id
stringlengths
4
5
url
stringlengths
39
537
title
stringlengths
2
65
text
stringlengths
2.04k
162k
22330
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8E%E1%8D%8B
ጎፋ
የጌዞ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጌዞኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። ሕዝብ ቁጥር በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ መልክዓ ምድር የዑባ ካቲ (ንጉሥ) ግዛት የዑባ አካባቢ ነፃ የተደራጀ ባህላዊ የፖለቲካ አስተዳደር የተፈጠረው ከአሪ ግዛት ተነጥሎ ዑባ ነፃ አስተዳደር ግዛት ከሆነበት ዘመን ወዲህ ነበር ። የዑባ ጥንታዊ ግዛት በሰሜን ዜንቲ ወንዝ : በደቡብ ምስራቅ የማዜ ወንዝ ይዞ እስከ ዛላና ዑባ መካከል ያለው ሸለቆ አልፎ ዘቃ ዛልቶ እና ጋላዳ ቀበለያትን ያካትታል ። በደቡብ ማሌ ወረዳ : በደቡብ ምዕራብ የአሪ ግዛት: በምዕራብ ሙሉ በሙሉ በአሪ ግዛት ይዋስናል ።የካቲው (የንጉሱ) አስተዳደር ሥርዓት ለብቻ የተዘረጋው ከአሪ ማዕከል የመጣው ንጉስ ሾዴ () ከነገሰበት ጊዜ ጀምሮ ሲሆን ይህንን ከላይ የተጠቀሰውን አካባቢ ይገዛ የነበረው የዚህ ትውልድ ነበር ። መጀመሪያ ከአሪ ወደ ዑባ አካባቢ የመጣው ሰው የተቀመጠው በዑባ ተራራማ አካባቢ አምፖ በሚል ስም በሚታወቅበት ቦታ ነበር ከዚህ በመነሳት የጎሳው ዝሪያዎች ቀስ በቀስ ግዛት አስፋፍተው ሊቆጣጠሩ እንደቻሉ ይገለፃል ። በአካባቢው የካቲ አስተዳደር ከተመሠረተ በኋላ ሰሜናዊ የግዛት ክፍል ማለትም መላና አካባቢውን : ጋልጣና አካባቢውን በመልቀቅ ወደ ደቡብ ምሥራቅ በማስፋፋት ጥንት የባዮ ግዛት የነበረውን ዙዛና አካባቢውን : ጋላዳና አካባቢውን ያዘ ። በሰሜናዊ ግዛት የጎፋ እና የዛላ ካቲ አይለው በነበሩ ጊዜ ዑባን በኃይል አስለቅቀው ወደ ደቡብ እንድዞር አደረገዋል ይባላል ። የጎፋ እና የዛላ ካቲታይ(ንጉሶች) ፍላጎት ከፍ እያለ በመጣበት ወቅት የዑባ ካቲ ላይ በጦርነት እነዚህን ቀበሌያትንና አካባቢውን በኃይል አስለቅቀው እንደያዘ ይነገራል ። ወደ ዑባ ተሻግረው ከነገሰው ሾደ() ነጥቀው በትውልድ ሀረግ ቆጠራ መሠረት የሚቀጥሉ ካቲዎች በዑባ ነግሰዋል:: 1. ጋልታይዛ 8. አይሳ 2. ሾጴ 9. ታንጋ 3. ፖሻ 10. ሉፀ 4. ቱጫ 11. ኦፈ 5. ቶልባ 12. ኩንሳ 6. ቦላ 13. ዲቻ ናቸው 7. ካንሳ ነበሩ ። እነዚህ ነገስታት ዑባን ከዳር እስከ ዳር ያስተዳደሩ የነበሩት አከባቢው ወደ ማዕከላዊ መንግስት አስተደደር ሥር እስከሚሆን ድረስ ነበር ። ዑባን ከገዙት ካቲዎች ውስጥ ድንበር ከማስከበር አልፎ ጦርነቶችን አካሄዶ የተወሰኑ ግዛት ክፍሎችን በኃይል እንደያዘ የሚነገረው ካቲ ቦላ ነበር ። ካቲ ቦላ በጣም ጦረኛ ስለነበረ ህዝብን አሰልፎ ከጎፋ እና ከዛላ ጋር በሚዋስኑ አካባቢዎች ድንበሮችን ለማካለል የበቃ ካቲ ነበር ። ከአሪ ግዛት ጋር ያለውን ውስጣዊ የዝምድና ትስስር በመበጠስ ወደ ጦርነት ገብቶ ድንበሩ እንድካለል ያደረገው እሱ እንደነበረ ይነገራል ። የዑባ ካቲ አስተዳደር ሥርዓት የጀመረው ከዑባ ዣላ ከፍ ብሎ በሚገኘው አምፖ በሚባለው ቦታ ነው ። እዚሁ መጀመሪያ መጥቶ የነገሰው ካቲው ሾዴ ሲሆን ሶስት የአምልኮ : የአስተዳደር ማዕከል እና የመኖሪያ ቦታዎችን በማበጀት ማስተዳደር ጀመረ ። በዚሁ መሠረት ዶጃ የነጋሲያን የአምልኮ ሥፍራ እና አምፖ የአስተዳደር ማዕከል ካምባ የመኖሪያ ቦታ አድርጎ በዚሁ ተራራ ላይ አዘጋጀ ። ከዚያን በኋላ ጥንታዊ የዑባ ግዛት ተብሎ የሚታወቀውን አካባቢ ይገዙ የነበሩ ካቲዎች ዋና መኖሪያቸውና የአስተዳደር ማዕከላቸውን እዚሁ አድርገዋል። ሆኖም ከኋላ አስተዳዳሩ እየተጠናከረ ሲሄድ ዣላ : ቡኔ : ጋልፃ እና በሌሎች ቦታዎች መቀመጫቻውን ያደረጉት የበታች ተሿሚዎችን ተጠርነቱን ለካቲው ሆኖ ሲያስተዳድሩ ቆይቷል ። ከላይ በተጠቀሱት የአስተዳደር አካበቢዎች ኃላፊነት ይዘው ያስተዳደሩት የነበሩ '' ማይጫ ዳና '' የሚል ማዕረግ ስም የያዙት ነበሩ ። በዚህ አቅጣጫ ካቲዎች ህዝብንና መሬትን በበላይነት ይመሩ እንደነበሩ የዕድሜ ባለፀጎች መረጃዎች ያስረዳሉ ። ሌላው ደግሞ ማይጫ ዳና ሥር የአስተዳደር ሥራዎችን ከመሥራት አኳያ ትልቅ አስተዋፆኦ እንደነበራቸው የሚነገርላቸው የሚባሉ ሳጋ እንደ ቃልቻ ያሉ ረግመውና መርቀው የሚያደርሱ ይገኙ ነበር ። ሥራቸውንም ሊያከናወኑ ህዝብ የከበረታ ሥፍራ ይሰጣቸው ነበር ። ሌሎች ደግሞ በህዝብ ውስጥ የሚሠሩ ባህላዊ አምልኮ አስፈፃሚዎች ብታንቴ የሚባሉት በየቀበሌያት ይገኙ ነበር ። በነፃ ግዛት ይኖር የነበረው ህዝብ በአዋሳኝ ከሚገኘው ህዝብ ጋር ተቀላቅሎ በጎሳ ሥርጭት : በባህል አንድ ሆኖ ኖረዋል ። ይሁንና የካቲ አስተዳደር እየተጠናከረ በሄደበት ወቅት ከጎፋም : ከዛላና ከሌሎች ደቡባዊ አቅጣጫ ከሚገኙት ጋር ጦርነቶችን አካሂደዋል ። ከዛላ ካቲ ግዛት ጋር መሀላ ፈጽመው የውል ስምምነቱን ጨርሰው የኖሩት ዑባ ዙማ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በተደረገው እርቅና ስምምነት ነበር ። በጎ ፋ ካቲ ካንሳና በዑባ ካቲ አይሳ መካከል ከፍተኛ ጦርነት በተካሄደበት ጊዜ በዑባ ጋይላ ላይ በተደረገው ውጊያ የመራውን ካቲ ካንሳን ወግቶ ካቆሰለ በኋላ እንደሞተ ይነገራል፡፡ በዚያን ዘመን በነዚህ አካባቢዎች ጦርነቶች ሲከፈቱ አንዱ ከሌላው ወገን ጋር ለማስታረቅ ጥረት የሚያደርጉት ራሳቸው ካቲዎች ነበሩ፡፡ ይህንን ሚና ካቲዎች የሚጫወቱት የሠላም ምልክት አድርገው በሚወስዱት የመልዕክት ልውውጥ ነበር፡፡ ይኽውም ቀድሞ ሰላም ፈላጊ ካቲው የራሱን መርኩዝ ለሌላኛው ካቲ በመላክና የዚያኛውንምርኩዝ የላከው መልዕክተኛ ይዞ ሲመጣ ነበር፡፡ ይህንን መጀመሪያ በመስጠትና ምላሽ የማግኘት ሥርዓት በመባል የሚታወቅ ሲሆን በዚህ ሁኔታ ሁለቱም ወገኖች ወደ እርቅ ድርድር ይገቡ ነበር፡፡ ካቲዎች ትልቅ አክብሮት ከህዝብ የሚሰጣቸው ሲሆን ሥልጣናቸውም ከመለኮታው ኃይል እንደሆነ አድርገው ይወስዱ ነበር፡፡ ስለዝህም ካቲው በዑባ በጣም ይከበራል፤ ህዝቡም ይታዘዝለት ነበር፡፡ የአነጋገስ ሥነ-ሥርዓትም በተመለከተ ለአጎራባች ካቲዎች እንደሚደረግላቸው ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም ለካቲዎች የሚደረግ ክብር መለክያ ዕቃዎች ተመሳሳይነት እና ካቲው ሲሞት የሚተካው የካቲው ታላቅ ልጅ መሆኑ ነው፡፡ ነገር ግን ሳጋ የሚባሉት ከሌሎች አንጋሾች ጋር በመሆን ካቲው በሚነግስበት ወቀት ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱት ክፍል እንደሆነ ይነገራል፡፡በዑባ የካቲ አስተዳደር መጀመር ተከትሎ በአጎራባች ከሚገኙት ካቲ ግዛቶች ጋር ያለው ግንኙት መልክ እየያዘ መጥቷል፡፡ቀደም ሲል በአከባቢው እንደነበሩ የሚነገሩ ጎሳው ተቋዋሚዎች ፈርሰው የአሪ ግዛት እየተጠናከረ እንደመጣ ብዛት ያላቸው ማህበረሰቦች በየቦታው በአይካ መንግሰት ሥር ሆነው ሲተዳደሩ ቆይቷል ፡፡ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የሚፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ‹‹ባጭራ›› የተባለው ምግባቸውና ‹‹ቅንጬ›› በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ጐፋዎች በነባሩ ባህላቸው ከቆፋ፣ ከሌጦና ከጥጥ የተሠሩ አልባሳትን ይጠቀሙ ነበር፡፡ ‹‹ኢቴ›› የማባለው ከቆዳና ከሌጦ የሚሠራውን ልብስ ወጣቶችና አዋቂዎች በጀርባቸው ላይ ጣል በማድረግ ከወገባቸው ብቻ ‹‹አሣራ›› (ዲታ) የሚባለውን ከጥጥ የሚሠራ ግልድም ያገለድማሉ፡፡ ማንቾ (ማሽኮ) ዕድሜያቸው ከ1-8 የማሆናቸው ሴት ሕፃናት ደሞ ከድርና ማግ አልፎ አልፎም ከቆዳ ተገምዶ ጫፉ ላይ በዛጎል ያጌጠን ልብስ ለብልታቸው መሸፈኛ ይታጠቁታል፡፡ በባህላዊ ሽመና የሚሠሩ ቡልኮ፣ጋቢ፣ነጠላ፣መቀነት ወዘተ… በብሔረሰቡ በብዛት የሚዘወተሩ አልባሳት ናቸው፡፡ የብሔረሰቡ አባል ሲሞት ለባህላዊ መዎች፣ ለአዛውንቶች፣ ለጎልማሶችም ሆነ ለወጣቶች ‹‹ዘዬና›› ‹‹ዳርበ›› የሚባለውን የሙዚቃ መሣሪያ በመምታት የአካባቢው ማኅበረሰብ እንዲሰበሰብ ይደረጋል፡፡ የሞተው ንጉሡ ከሆነ ሁሉም ሰው ግንባሩን ጥላሸት ወይም ጭቃ በመቀባት በፀጉሩ ላይ ደግሞ አመድ በመነስነስ ‹‹ሰማይ ተናደ›› በማለት ያለቀሳል፡፡ የለቅሶው ርዝማኔ እንደሟች ክብርና ዝና ከ4-7 ቀናት ይቆያል፡፡ ታዋቂ ሰዎች ጎፋ የኢትዮጵያ ብሔር ነው። የኢትዮጵያ ብሔሮች
53925
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9A%E1%8A%95%E1%8C%8A
ሚንጊ
ሚንጊ ማለት በደቡባዊው የኢትዮጲያ ክፍል በተለይም በኦሞ ወንዝ አካባቢ ኑሯቸውን ባደረጉ የኦሞ እና የሀመር ህዝቦች የሚዘወተር ባህላዊ ልማድ ነው። በባህሉ መሰረት ሚንጊ ናቸው ተብለው የተፈረጁ ልጆች ንጹህ እንዳይደሉ እና በማህበረሰቡም ላይም እርግማን ያመጣሉ ተብሎ ይታሰባል። ከዚህም የተነሳ የተለያዩ እርምጃዎች ህጻናቱ ላይ ይደርስባቸዋል። አንድ ህጻን ሚንጊ ነው የሚባለው ከታችኛው ጥርሱ ቀድሞ የላይኛው ጥርሱ ከበቀለ፣ ልጆቹ መንታ ሆነው ከተወለዱ እንዲሁም ከጋብቻ ውጪ የተወለዱ ልጆች ሲሆኑ ነው። ሳይንሳዊ ጥናት እና ምርምሮች እንደሚያሳዩት የህጻን ልጆች ጥርስ የአንዳንዱ የላይኛው ቀድሞ ሲበቅል የአንዳንዱ ደግሞ ታችኛው ቀድሞ ይበቅላል። ይህም በልጆቹ ጤንነት ላይ የሚያሳድረው ምንም አይነት አሉታዊ ተጽዕኖ የለም። መንታ ልጅ መውለድም ቢሆን እርግማን አይደለም። የጎሳ መሪ የሆኑ ሰዎች በአካባቢያቸው ሚንጊ የሆነው ልጅ እንዳለ ካወቁ ቶሎ ብለው መጥተው ልጁን ወደ ጥልቅ ጉድጓድ ወይም ወንዝ በመወርወር ፣ አፉ ውስጥ ብዙ አፈር በመጨመር እንዲሁም ህጻኑን ጫካ ውስጥ በመጣል ህይወቱ እንዲያልፍ ያደርጋሉ። በዚህ ባህል እጅግ በጣም ለዉጥር የሚታክቱ ብዙ ህጻናት ተሰውተዋል። ሚንጊ ናቸው ተብለው ከሚፈረጁት ህጻናት ባለፈ የአካል ጉዳተኛ ሆነው የሚወለዱ ወይም ከተወለዱ በኋላ በለጋ እድሜያቸው የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ህጻናትም ይሄው እጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ የሚሞቱ ህጻናት ስርዓቱን የጠበቀ የቀብር ስነ ስርዓት እንኳን አይደረግላቸውም። ሚንጊ እንደሆኑ እንደታወቀ የጎሳው መሪ አካላት ወደ ቤታቸው በመሄድ ህጻናቱን ከእናታቸው እጅ ነጥቀው በመውሰድ ህይወታቸው እንዲያልፍ ያደርጋሉ። መቼ እና እንዴት ተጀመረ? ይሄ ባህል መቼ እና እንዴት እንደተጀመረ በውል የሚታወቅ ነገር ባይኖርም ነገር ግን በተለያየ ምክኒያት ለአካባቢው ማህበረሰብ ጥንክሮ በመስራት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ ማይችሉትን ለመቀነስ ታስቦ የተጀመረ ባህል እንደሆነ አንዳንዶች መላ ምታቸውን ያስቀምጣሉ። ከዚህ መላ ምት ያለፈ የተጻፈ እና የተሰነደ ስለ ባህሉ ታሪካዊ አመጣጥ የሚገልጽ የታሪክ መዝገብ የለም። ሆኖም ግን ለረዥም ጊዜያት ሲተገበር እንደኖረ ግልጽ ነው። በዚህ ባህል ምንም የማያውቁ ህጻናት ገና ምንም ሳያውቁ እርግማን ታመጣላችሁ በሚል ሰበብ ህይወታቸው እንዲያልፍ ይደረጋል። እናቶችም ለዘጠኝ ወራት በሆዳቸው ተሸክመው፣ በብዙ ስቃይ አምጠው ወልደው፣ አጥብተው ያሳደጉትን ልጅ የጎሳቸው መሪዎች በጉልበት ነጥቀው ወስደው አይናቸው እያየ በሚዘገንን ሁኔታ ጭካኔ በተሞላው መንገድ ሲሞቱ ማየት ቀላል ነገር ሊሆንላቸው አይችልም። ከዚሁ ጋር ተያይዞም ከፍተኛ የሆነ የሞራል ጉዳት እና ስብራት ይደርስባቸዋል። ሆኖም ባህሉ እጅግ ስር የሰደደ እና በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘ ስለሆነ ልጃቸውን በእምባ ከመሸኘት በስተቀር አማራጭ የላቸውም። እንደ አውሮፓዊያኑ የዘመን ቀመር ከ1936 - 1947 ዓ.ም ባለው ጊዜ ጣሊያን ኢትዮጲያ የኔ ግዛት ናት ባለችበት ወቅት በምስራቅ አፍሪካ የኢጣሊያ ግዛት ናቸው በተባሉ ቦታዎች ሁሉ ላይ መሰል ድርጊቶች እንዳይደረጉ አግዳ ነበር። በዚህ መቀትም ሚንጊ ናቸው ብሎ ልጆችን መፈረጅ እና ህይወታቸው እንዲያልፍ ማድረግ እንደ ትልቅ ወንጀል ይቆጠር እና ያስቀጣ ነበር። ከብዙ አመታት በኋላም በ2012 ዓ.ም የካሮ ህዝቦች ሚንጊ የሚለው ባህል መቀረት እንዳለበት ስምምነት አድርገው ነበር። ሆኖም ይሄው ስምምነት በተፈለገው ደረጃ መሬት ላይ ሊወርድ አልቻለም ነበር። አሁን ድረስም ከ680,000 ያላነሱ የማህበረሰቡ አካላት ይህንኑ ጎጂ የሆነ ባህል እንደሚተግብሩት ይታወቃል። የማስቆም ሂደት ላሌ ላቡኮ የተባለ የካሮ ጎሳ ተወላጅ ገና የአስራ አምስት አመት ልጅ እያለ ሚንጊ ነው ተብሎ በማህበረሰቡ የተወገዘ ህጻን ልጅ ሲገደል በማየቱ እጅግ በጣም አዝኖ ነበር። ላሌ ከዚህ ፣አህበርሰብ ከተገኙ ሰዎች መካከል በሚሽነሪ ትምህርት ቤቶች የመማር እድል ያገኘ ልጅ ነበር። ካደገ በኋላም እ.ኤ.አ በ2012 ዓ.ም አንዲት ህጻን ወላጆቿ በትዳር ሳይጣመሩ የወለዷት በመሆኗ ብቻ ልትገደ እያለ የሚችለውን ሁሉ በማድረግ ህይወቷን ያተረፋል። ከዚህም በኋላ ቀስ በቀስ እንደዚህ ሚንጊ የተባሉ ልጆችን ከሞት በማትረፍ እና ወደ ከተማ በመወሰድ ለህጻንቱ የሚሆን መጠለያ ስፍራ በማዘጋጀት ያሳድጋቸው ጀመር። ይሄ በጎ ስራውም ቀስ በቀስ እየተሰማ ሄዶ የዚህን ህዝብ ታሪክ እና የእርሱን መልካም ስራ የሚዘክሩ ሁለት ዶክመንታሪዎች ተሰርተዋል። የመጀመሪያው የሚል እና በ2012 የተሰራ ሲሆን ከዚህ በመቀጠልም በ2015 ዓ.ም ጆን ሮው () በሚባል እውቅ ፊልም ፕሮዲዩሰር አማካኝነት የሚል ዶክመንታሪ ተሰርቶ ለእይታ በቅቷል። ዶክመንታሪዎቹም ሽልማትን አግኝተው ነበር። ከጊዜያት በኋላም ላሌ ከፕሮዲዩሰሩ ጋር በመሆን የኦሞ ልጆች ድርጅትን ከፍተው ህጻናትን ከሞት ለማትረፍ እየሰሩ ይገኛሉ። በ ር አጋዥነት ለዚሁ አላማ በተሰራ መጠለያ ቤት ውስጥም ወደ 50 የሚደርሱ እድሜያቸው ከ 1 እስከ 11 የሆነ የእድሜ ክልልየሚገኙ ህጻናት ከሚንጊ ሞት ተርፈው ይኖራሉ።
1840
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A4%E1%88%AD%E1%89%B5%E1%88%AB
ኤርትራ
ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን: በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲኑ «» የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪኩ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። አካባቢው( ከ1890 በፊት) ክዴቭ ፓሻ በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። ሦስቱ ማዕከላት ግብጾቹ አካባቢውን ለቅኝ ግዛታቸው ብለው አንድ ከማድረጋቸው በፊት በዚህ መልክዓ ምድር ሦስት እራሳቸውን የቻሉ ማዕከላት በታሪክ ይጠቀሳሉ። ታሪክ አጥኝው ካህሳይ ብርሐኔ እኒህን ሦስት ማዕከላት የጋራ ታሪክ የሌላቸው፣ ኢ-ጥገኛ ህዝቦች ይላቸዋል። የመጀመሪያው ማዕከል በምዕራብ ቆላማ ክፍል የሚገኘው ሲሆን፣ ከመልክዓምድር አንጻር ከከሰላ እስከ ቦጎስ ያለውን ቦታ ያካልላል። በተለምዶ ባርካ የሚባለው ነው። ይህ ክፍል ትግረ ቋንቋ በሚናገሩ የቤኒ አሚር ጎሳዎች የሚመራ ቢሆንም በውስጡ ሌሎች ብሔሮችን አጠቃሎ ይዟል። አካባቢው ከደጋው የአሁኑ ኤርትራ ክፍል ይበልጥ ከሱዳኖች ጋር የበለጠ ጥብቅ ትሥሥር ነበርው። ለዚህ ምክንያቱ በ1820ዎቹ ሚርጋኒያን የእስልምና እምነትን ለቤኒ አሚሮች በመስበክ ስላስፋፉ ነበር። ሚርጋኒያ ወየም የሚርጋኒያ ቤተሰቦች ከሰላ ውስጥ ሃትሚያ በተባለ የሱፊ እስልምና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ የአንድ ቤተሰብ ሰወች ነበሩ። ሁለተኛው ማዕከል ከምዕራቡ ክፍል በቋንቋም ሆነ በብሔር በጣም የተለየ ነው፣ የሚገኘውም በስተምስራቅ፣ በቀይ ባሕር ጠረፍ አካባቢ ነው። መጀመሪያ ደረጃ፣ ይህ የጠረፍ አካባቢ በስመ አዱሊስ የአክሱም ዋና ግዛት ነበር። ሆኖም ከ8ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ አካባቢው በእስልምና ምህዋር ስር በመውደቁ (የዳህላክ ሡልጣኔት፣ ለምሳሌ)፣ ከመካከለኛው የኢትዮጵያ ግዛት አፈነገጠ። ምንም እንኳ የኢትዮጵያ ነገሥታት (ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ለምሳሌ) አልፎ አልፎ አካባቢውን በማስመለስ በባሕር ምድር ስም የባሕረ ነጋሽ ግዛት አድርገው ቢያስተዳድሩትም ከ8ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የያዘውን መልክ ሊቀይር አልቻለም ። የዚህ አካባቢ ዋና ማዕከል ምፅዋ የነበረ ሲሆን በምጽዋ አረቦች ቤታቸውን ሰርተው የእስልምና ማዕከል አድርገውት ነበር። ይህን የእስልምና ማንነት በሚያፀና መልኩ ኦቶማን ቱርኮች ምጽዋን ከ1557 እስከ 1578 ባደረጉት ዘመቻ ተቆጣጥረው የቀይባሕር እስላማዊ ቅኝ ግዛታቸው አካል አደረጉት። በአካባቢው በረሃወች የሚኖሩት አፋሮች የእስልምናን ስርዓት መያዝ የጀመሩት በዚሁ ዘመን፣ በ16ኛው ክፍለ ዘመን ነበር። ሦስተኛው ማዕከል በሁለቱ መሃል የሚገኘው ተራራማው የሐማሴን፣ ሰራየ እና አካለ ጉዛይ ግዛት ሲሆን በዚህ ቦታ ትግርኛ ተናጋሪ ክርስቲያኖች ይገኙበታል። በተለምዶ መረብ ምላሽ የሚባለው ነው። ይህ ክፍል ከጥንት ጀምሮ የኢትዮጵያ ዋና ክፍል የነበረ ነው። በአክሱም ዘመነ መንግስት የግዛቱ አይነተኛ ክፍል፣ እንዲሁም የሥርዓተ ገዳምና የክርስትና ዋና ማዕከል ነበር። ከአክሱም በኋላም ባሕር ምድር ተብሎ የሚታወቀው ግዛት ዋና እምብርት ነበር። ክፍሉ በኢትዮጵያ ከሚገኘው ሌላው የትግርኛ ተናጋሪ ጋር ካለው ቁርኝት አንጻር የሚለየው የነበር በሁለቱ ክፍሎች መካከል በሚጓዘው መረብ ወንዝ ነበር። ስለሆነም መረብ ምላሽ ተብሎ ይታወቅ ነበር። እንደማንኛው ሌላው የኢትዮጵያ ክፍል፣ የዚህ አካባቢ ታሪክ የሚያጠነጥነው ከመካከለኛው የኢትዮጵያ መንግስት ጋር በነበረው ግንኙነት ዙሪያ ነበር። የመረብ ምላሽ ዋና ክፍል ሐማሴን ሲሆን ይህ ክፍል ለዘመናት ይተዳደር የነበረው በሁለት ተፎካካሪ ቤተሰቦች ነበር፡ እነርሱም ሓዛጋ እና ሳዛጋ በመባል ይታወቃሉ። ይህ ክፍል አንድ አንድ ዘመቻወችን ወደ ቆላው ቢያደርግም፣ አልፎ አልፎም ከውጭ ሃይሎች እርዳታ ቢያገኝም፣ በአጠቃላይ ግን የአስተዳደሩ ስርዓት ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵያዊ ባህልንና ትውፊትን የተከተለ ነበር። አጼ ዮሐንስ፣ ግብጾች፣ መሃዲስቶች እና ጣሊያኖች ይህ በዚህ እንዳለ ነበር ግብጾች (ክዴቭ ፓሻ) እኒህን ሶስት ክፍሎች አንድ በማድረግ ከኢትዮጵያ ለይተው ለመግዛት የሞከሩት። ከላይ እንደተጠቀሰው ግብጾች ከከሰላ ምጽዋ የሚዘልቀውን መንገድ ቅኝ አድርገው ነበር ሆኖም ግን ለጸጥታ ሲሉ የደጋውን ክርስቲያን ክፍል ለመቆጣጠር ሞክሩ። በዚህ ምክንያት ከኢትዮጵያ ጋር ጦርነት ገቡ። በኖቬምበር 16፣ 1875 ላይ የአጼ ዮሐንስን ሰራዊት ጉንደት በተባለ ቦታ ገጥመው ተሸነፉ። ማርች 1-9፣ 1876 ላይ እንደገና ጉራ በተባለ ቦታ ገጥመው ከፍተኛ ሽንፈት ገጠማቸው። ይህን አይነት ክስረት ከገጠማቸው በኋላ ደጋውን ክፍል ትተው ድሮ በነበሩበት ምጽዋ-ከሰላ፣ በተለይ ቦጎስ ፣ መንገድ ላይ ተወሰነው በኢትዮጵያውያን ላይ የደፈጣ ውጊያ ማድረግ ቀጠሉ። ጠንክረው ለመከላከል ሲሉ፣ አጼ ዮሐንስ መረብ ምላሽን ለመያዝ አሰቡ፤ ስለሆነም በ1876 ዓ.ም. ራስ አሉላ እንግዳን የመረብ ምላሽ ገዥ አድርገው ሰየሟቸው። ራስ አሉላ በአገሬው ሰው እንደ ጸጉረ ልውጥ ተደርገው በመቆጠራቸው ነገሩ ቅሬታን ፈጠረ። ስለሆነም የመረብ ምላሽ የቀደመ ገዥ የነበሩት ራስ ወልደሚካኤል በግብጾች እርዳታ ሐማሴንን ለተወሰነ ጊዜ መቆጣጠር ችለው ነበር። ራስ ወልደሚካኤል በ1879 ተማርከው ለእስር ተዳረጉ። ነገሮች እንዲህ ከተደላደሉ በኋላ ራስ አሉላ በግብጾች ምሽጎች ላይ አልፎ አልፎ ዘመቻ በማድረግ ጥቃት ማድረስ ጀመሩ። በመካለሉ ማሃዲ ሱዳኖች በግብጾች ላይ በመነሳታቸው ግብጾች ከሁለት ጎን አጣብቂኝ ውስጥ ገቡ። ከአጣብቂኙ ለመገላገልና ከአካባቢው በሰላም ለመውጣት ሲሉ ግብጾቹ በ1884 ከአሉላ ጋር የሄዌት ስምምነት የተባለውን ውል ተፈራረሙ። ብዙም ሳይቆይ፣ ከአመት በኋላ፣ ታኅሣሥ 1885 ላይ ጣሊያኖች ምፅዋ ላይ መልህቃቸውን ጥለው ወደ መሃል መስፋፋታቸውን ጀመሩ። መስከረም 1885 ላይ አሉላና የሱዳን መሃዲስቶች ኩፊት በተባለ ቦታ ተገናኝተው ራስ አሉላ ጦርነቱን በድል ቢደመድሙም ከሰላን ለመቆጣጠር የነበራቸው እቅድ በጣሊያኖች ወደ ምጽዋ ዘልቆ መግባት ተዘናጋ። ፊታቸውን ከምዕራቡ ግንባር በመመለስ፣ ራስ አሉላ፣ ጣሊያኖችን በዶገሊ ጦርነት እንዲሁም በኮዓቲት ጦርነት ድል አደርጓቸው። ይሁንና የጣሊያኖች መስፋፋት ሊገታ አልቻለም። ለዚህ ምክንያቱ በምዕራብ የመሃዲስቶች ጦርነትና እንዲሁም የጣሊያኖች በሃይል መጠናከር ነበር። በኒህ ድርብ ጫናዎች ምክንያት 1888 ላይ የኢትዮጵያ ሠራዊት አፈግፍጎ መረብ ወንዝን ተሻገረ። 1889 ዓ.ም. ያለመንም ጦርነት የጣሊያን ሰራዊት አስመራ ገባ። እንግዲህ በዚህ ዘመን የተፈጠረው የምዕራብ ኤርትራ(ባርካ)፣ የምጽዋዕ እስላሞች፣ የሱዳንና የግብጽ ግንኙነት ነበር በኋላ በ1950ወቹ ለተነሳው የኤርትራ ነጻነት ግንባር ጀብሃ የሚለውን አላማ መሰረት የሆነው። የኤርትራ ህዝቦች ነጻነት ግንባርም የአሉላን ጸጉረ ልውጥነትና በህዝቡ ዘንድ ያስነሳውን ማንጎራጎር እንደ-የመረብ ምላሽ ህዝብ ነጻነት ጥያቄ መነሻ አድርጎ ይወስደዋል። ይህ የታሪክ ክፍል የቱን ያክል ለ20ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያና የኤርትራ ታሪክ ሚና እንደነበረው ለመገንዘብ አዳጋች አይደለም። ኮሎኒያ ኤርትራ የጣሊያኖች መስፋፋት የጣሊያን መንግስት በደቡብ ምዕራብ ቀይ ባህር ጠረፍ ላይ ከአንድ የመርክብ ኩባንያ ቦታዎችን በመግዛት በመሬቱ ላይ የሕጋዊ ይገባኛልን አጸና። እንዲሁም ከአካባቢው መሪዎች ጋር ውል በመፈራረም አሰብንና ቅርብ ደሴቶቿን ሐምሌ 1882 ቅኝ ግዛቶቹ እንደሆኑ አወጀ። ይህ እንግዴህ ኮሎኒያ አሰብ የሚባለው ነው። ከሶስት አመት በኋላ፣ የካቲት 1885 በእንግሊዞች መልካም ፈቃድ ምፅዋን ከግብጾች በመንጠቅ ተቆጣጠረ። ቀጥሎም ከጎጥ መሪዎች ጋር ውሎች በመፈራረም ሰምሐር እና ሳህል የሚባሉትን የሰሜን ምዕራብ ክፍሎች በሰላማዊ መንገድ ወደ ግዛታቸው ጠቀለሉ። ወደ ደቡብ ግን በጦርነትና ክፋፍሎ ማሸነፍ በሚለው የቅኝ ግዛት መንገድ መስፋፋት ጀመሩ። የመሃዲስቶችን፣ ኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያውን መካከል ያለውን ፉክክር በመጠቀም ሐማሴንን፣ ሰራየንና አካለ ጉዛይን ገንዘባቸው አደረጉ። ዳግማዊ አጼ ምንሊክ የአጼ ዮሐንስ ተተኪ ንጉስ እንዲሆኑ በመርዳት በቀይ ባህር ጠረፍ ላይ ያላቸውን ግዛት ህጋዊነት እንዲቀበሉ አደረጉ (የውጫሌ ውል)። የውጫሌን ውል፣ አንቀጽ 3፣ የጣሊያኖችን ግዛት በምስራቃዊው ጠለል ላይ የወሰነ ቢሆንም እነርሱ ግን ውሉን በመጣስ ግዛታቸውን እስከ መረብ ወንዝ ድረስ አስፋፉ። 1890 ላይ ይህን ግዛታቸውን ኤሪትራ ብለው ሰየሙት። በጊዜው፣ የኤርትሪያ ሕዝብ ስብጥር ኤርትራን ካወጁ በኋላ ጣሊያኖች በ3ኛው አመት ህዝብ ቆጠራ አደረጉ። በዚህ ወቅት የህዝቡ ብዛት 191፣127 እንደሆነ ሊታወቅ ቻለ። በዘመኑ ከአርሶ አደሩ ክርስቲያን ደገኛ ትግርኛ ተናጋሪዎች በተጨማሪ በምዕራብ፣ ዘላን መስሊሞች ፡ ቤኒ አሚር፣ ብሌን፣ ሐባብ፣ መንሳ እና ማርያ እንዲሁም ዘላንና አርሶ አደር የሆኑት ኩናማና ናራ የተሰኙ ብሔሮች እንደሚኖሩ ታወቀ። በምስራቅና በደቡብ የባህር ጠረፎች ደግሞ አፋርና ሳሆ የተሰኙ አርብቶ አደሮች እንደሚኖሩበት ተመዘገበ። የጣሊያኖች አገዛዝ ጣሊያኖች የግዛታቸውን ማዕከል ምፅዋ ላይ በማድርገ የቢሮክራሲ ስርዓት ዘርግተው በራሱ ላይ ወታደራዊ ገዥወች ሾሙበት። ቆይተውም ከአገሬው ወሰደው 300+ሺህ ሄክታር የሚሆነውን መሬት ለአውሮጳውያን ገበሬዎች ለመስጠት ያሰቡት እቅድ ከህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ደርሶበት ተቋረጠ። ሚያዚያ 1894 በደጃዝማች ባህታ ሐጎስ የተነሳው አመጽ ጣሊያኖች ወደ ኢትዮጵያ፣ ትግራይ የማጥቃት ጦርነት እንዲከፍቱ አደረገ። ነገር ግን በዳግማዊ ምኒልክ የተመራው የኢትዮጵያ ሰራዊት ጣሊያኖችን በተደጋጋሚ ድል አደረጋቸው (አምባላጌ-ታህሳስ 1895፣ አድዋ - መጋቢት 1896)። በኒህ ጦርነቶች ጣሊያኖች ወደ 10፣000 ወታደሮችና 500 ሚሊዮን ሊሬ በመክሰራቸው ከዚህ በኋላ ለቅኝ ግዛታቸው የሚያወጡትን ወጭ ቀነሱ።በዚህ ጦርነት የማይረሳው ብዙ ወታደሮችም ተማርኳል የጣልያን ምርኮኛችን በካሳ እንዲለቀቁ ተስማምቷል ለኤርትራውያን የጣልያን ወታደሮች ግን ኣንድ እግራቸው እና ኣንድ እጃቸውን በመቁረጥ እንዲለቀቁ ተደርጓል የማይረሳው የኢትዮጵያ ጥቁር ታሪክ የነበረውን ጸብ ከዚህ ይጀምራል፣ከዚያ ወዲህ ጣልያኖች ከኢትዮጵያ ጋር መልካም ጉርብትና ፈለጉ እንጂ በቀደመው አጥቂነታቸው ለመቀጠል አልፈለጉም። ጣሊያኖች ግዛታቸውን አጸኑ ከአድዋ ሽንፈት በኋላ ጣሊያኖች ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራርመው አዲስ ገዢ፣ ፈርዲናንዶ ማርቲኒ፣ 1897 ላይ በመሾም ግዛታቸውን ማጽናት ጀመሩ። በዚህ ወቅት የቀደመው ወታደራዊ ስርዓት እንዲቋረጥ ተደርጎ አገሪቱ የብሔር ልዩነትን "በሚያከበር" አስተዳደር ተከፍሎ እንዲቋቋም ተደረገ። ዳህላክ፣ አፋር እና ሰምሃር አንድ ላይ "ምስራቃዊ ክፍል" ተብለው ከምጽዋ እንዲተዳደሩ ተደረገ። "ምዕራባዊ ክፍል" ከአቆርዳት እንዲተዳደር ሲደረግ ቤኒ አሚርን፣ ናራንና ኩናማ ምድርን ያጠቃልል ነበር። ከከረን ሆኖ የሚተዳደረው ደግሞ ሰሜናዊ ሐማሴን (የእስልምና ተከታይ የሆነ)፣ ቤት አሰገደና ዓድ ሼኽ ነበሩ። ቀሪው ሐማሴን ከአስመራ፣ ሰራየ ከመንደፈራ(አዲ ወግሪ) እንዲተዳደር ሲደረግ አካለ ጉዛይ ከሳሆ ጋር ተዋህዶ ከአዲ ቀይሕ ይገዛ ጀመር። ከላይ ወደታች በተዘርጋ መዋቅር የጣሊያን ባለስልጣኖች እያንዳንዱን ክፍል ያስተዳድሩ ጀመር። የአገሪቱ ዋና ከተማ ከምጽዋ ወደ አስመራ የተዛወረው በዚህ ወቅት፣ በ1898 ነበር። ከ1898 እስከ 1908 በተደረጉ ውሎች (ከኢትዮጵያ፣ ከአንግሎ-ግብጻዊ ሱዳንና ከጅቡቲ ጋር) መሰረት የቅኝ ግዛቱ ድንበር ታወቀ። ኢትዮጵያን ስለ ድንበሩ ለማሳመን 3 አመትና 5ሚሊዮን ሊሬ ፈጅቶባቸው ግንቦት 1900 ላይ ያሰቡት ሊሳካላቸው ቻለ። ድንበሩ ከሞላ ጎደል የመረብ፣ በለሳና ሙና ወንዞችን የታከከ ነበር። የቅኝ ግዛቱ አስተዳደር በ1898 ጣሊያኖች ለቅኝ ግዛታቸው አዲስ ደንብ አወጡ። ድሮ ይጠቀሙበትን የነበረውን የአገሬውን ባላባት በጭካኔ የመቅጣት መንገድ በመተው፣ ከነሱ ጋር የተሻረከውን የመሸለምና በነሱ ስር እንዲሰራ የማድረግ ዘዴን ጀመሩ። ከሕግም አንጻር የጣሊያን ሕግ ለጣሊያን ገዥወች የሚሰራ ቢሆንም የአካባቢው ሕግ ( ለምሳሌ የሙስሊሞች ሕግ) ለአካባቢው ሕዝብ እንዲሰራ አደረጉ። ከላይ ጣሊያኖች የሁሉ ገዢወች ሲሆኑ ከስር የአካባቢውን መሪወች ቀጥረው እንዲያስተዳድሩ አደረጉ። የአካባቢው ገዥወች ግብር በመሰብሰብ፣ ሕግ በማስከበርና ፍርድ በመስጠት ያገለግሉ ነበር። ይህ የአገሩን መሬት በአገሩ በሬ ዘዲያቸው የተሳካ ከመሆኑ የተነሳ በዚህ ወቅት አገሬው በአመጽ እንዳይነሳ እረድቷል፣ ቢነሳም በጣም በአናሳ ሁኔታ አልፎ አልፎ ነበር (ለምሳሌ ደጃዝማች አበራ ግዛው፣ ሙሃሙድ ኑሪና ገብረመድህን ሐጎስ ወደ ኢትዮጵያ እንዲሸሹ የተገደዱ)። ጣሊያኖቹ በዚህ ዘመን ትግርኛ ከማይናገረው ክፍል ከፍተኛ ድጋፍን አገኙ፣ ለዚህም ምክንያቱ ሕግና ሥርዓት ባሉት መመሪያቸው መሰረተ ከደጋው ወደነዚህ ክፍሎች የሚመጣውን ዘመቻ በማስቆማቸው ነበር። በወቅቱ የጣሊያኖች ዋና አላማ ፖለቲካዊ መረጋጋት ስለነበር የትግርኛ ተናጋሪውን ክፍል በአመጽ እንዳይነሳ ብዙ ስራ ሰርተዋል። ስለሆነም የትግርኛውን ክፍሎች ማህበረሰባዊ ትሥሥር ለመቆራረጥ ብዙ ሙከራወችን አድርገዋል። የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን ለተግባራቸው እንዲረዳቸው በእጅጉ ሞክረዋል። ነገር ግን ይህ ሙከራቸው ብዙ ፍሬ አላፈራም። ጣሊያኖቹ የእስላምና ተከታዩን ክፍል ድጋፍ ለማግኘት ሲሉ የእስልምና ሃይማኖትን መስፋፋት በሰፊው ይደግፉ ስለነበር። በዚህ ምክንያት የኦርቶዶክስ ተከታዩ ክፍል የካቶሊክ ቤተከርስቲያንን በመጥፎ አይን በመመልከት የትግርኛ ተናጋሪውን ህዝብ ወደ ካቶሊክ ሃይማኖት የመግባት ፍላጎት እጅግ አነስተኛ ሆነ። እንዲያውም የኦርቶዶክሱ ቤተክርስቲያን ከኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጋር በነበረው ጥብቅ ግንኙነት ምክንያት ከ1920ወቹ ጀምሮ ለቅኝ ገዥወቹ ከፍተኛ ተቃውሞ ይመጣ የነንበረው ከኒሁ አብያተ ክርስቲያናት ሆነ። የትምህርት ፖሊሲ አብላጫው የትምህርት ስራ በካቶሊክና በፕሮቴስታንት ሚስዮናውያን የሚሰራ ነበር። በመጀመሪያ፣ የአገሬው ህዝብ ዕውቀት አድማሱ እንዳይሰፋ በማሰብ እንዳይማር በህግ ተከልክሎ ነበር ። ነገር ግን ለቅኝ ግዛቱ ተላላኪዎች ለመፍጠር በማስብ አገሬው አንስተኛ የኢለመንታሪ ትምህርት እንዲማር ተፈቀደ፣ ይሄውም የሆነው በ1911 ነበር።ከ 1ኛ ክፍል እስከ 4ኛ ክፍል ነበረ፣ ጣሊያኖቹ በተጨማሪ በአስቀመጧቸው የተለያዩ መሰናክሎች ምክንያት አቅማቸው ለትምህርት ከደረሱ የአገሬው ሰዎች መካከል ከላይ የተጠቀሰውን ትምህርት ያገኙት ከ2% አይበልጡም ነበር። ቅኝ ግዛቱ፣ ኤርትራዊ ምሁር እንዳይኖር ማድረጉ የማይካድ ሃቅ ነው። ጣሊያኖችና አገሬው በኤርትራ ኗሪ የሆኑ ጣሊያኖች ቁጥር ቀስ በቀስ እያደገ ሄዶ 1934ዓ.ም. ላይ 4፣500 ደርሶ ነበር። በሚቀጥሉት 5 አመታት ከፍተኛ እድገትን በማሳየት፣ 1939ዓ.ም. ላይ ቁጥራቸው 75፣000 ደርሶ ነበር። ከሰፋሪ ጣሊያኖቹ ውስጥ የፋብሪካ ባለቤቶችና ገበሬዎች ቢገኙበትም አብዛኞቹ ግን መኖሪያቸውን ያደረጉት በአስመራና ምጽዋ ነበር። በ1930ወቹ መጨረሻ ላይ አንድ-አምስተኛ የሚሆኑት የአገሬው ሰዎች በከተማ ይኖሩ ነበር። በአንስተኛ ደመዎዝ እየሰሩ፣ ለአገሬው በተዘጋጁ የከተማ ክፍሎች ተወስነውና የፖለቲካ አቅም እንዳይኖራቸው የጣሊያን ዜግነት ተነፍጓቸው ይኖሩ ነበር። የአፓርታይድ ስርዓት እና ፋሽዝም ምንም እንኳ በቅኝ ግዛት ስርዓት መሰረት አገሬውና ገዥዎቹ እኩል ባይታዩም እስከ ፋሽዝም መነሳት ድረስ የአገሬው ህዝብና ጣሊያኖቹ ከሞላ ጎደል የመደባለቅ ሁኔታ አሳይተዋል። ነገር ግን በ1930ዎቹ መጨረሻ ላይ አይን ያወጣ የአፓርታይድ ዘረኝነት ተጀመረ። በኤውሮጳውያንና በአገሬው ህዝብ መካከል ማንኛውም አይነት ጋብቻም ሆነ አብሮ መኖር በህግ ተከለከለ። 1940 ላይ የጣሊያንና አገሬው ክልሶች ሳይቀሩ የዜግነትና የትምህርት መብታቸውን በህግ አጡ። የኢኮኖሚ እድገትና የልዩ ማንነት መፈጠር ከ1936 ጀምሮ ኤርትራ የኢኮኖሚ እድገት ማሳየት ችሏል። በ30ዎቹ መጨረሻ 2፣198 የኢንደስትሪ ተቋሞች በአገሪቱ ተመስርተዋል። ይሁንና ጣሊያኖች አገሪቱ እራሷን እንድትችል ሳይሆን የነርሱ ጥገኛ እንድትሆን ነበር ያደረጉት፣ ለዚህ ሲሉ አብዛኛው ምርት ከውጭ ያስመጡ ነበር። ከ10-15% የሚሆነው የአገሬው ወንድ ሃይል በኢንደስትሪ፣ በእርሻና በጥቃቅን የተላላኪ ስራወች ተቀጥርው ይሰሩ ነበር። ከ1936-41 ድረስ አብዛኛውን የአግሬውን ወንድ ቀጥሮ ያሰራ የነበረው የቅኝ ገዥው ውትድርና ተቋም ነበር (40% ወይም 60፣000 ለአቅመ አዳም የደርሱ ወንዶችን)። እኒህ ወታደሮች ኢትዮጵያን ለመውረር ያገለገሉ ሲሆን ለዚህ ታማኝነታቸው ምክንያቱ ቅኝ ገዥወች በኤርትራ ላይ ያሰፈኑት ፖለቲካዊ መረጋጋት እንደምክንያት ይጠቀሳል። የጤና፣ የገበያ ኢኮኖሚ እንዲሁም ቁሳዊ ፍጆታ መስፋፋት በ1905ዓ.ም. 250 ሺህ ብቻ የነበረው የኤርትራ ህዝብ ወደ 614 ሺሕ በ1935 ዓ.ም. እንዲያድግ አድርጓል። ትግርኛ ተናጋሪው ክፍል በዚህ ጊዜ 54% የአገሪቱ ክፍል ነበር። እኒህ ለውጦች በአገሬው ላይ የስነ ልቦና ለውጥን አስከተሉ፣ ስለሆነም ከኢትዮጵያውያን ጐረቤቶቻቸው የተለዩ ህዝቦች የመሆን ማንነትን ፈጠረ። የእንግሊዝ ወታደራዊ አገዛዝ ሁለተኛው የአለም ጦርነትን ተከትሎ እንግሊዞች ከአንግሎ ግብጻዊ ሱዳን በመነሳት ጥር 1941 በኤርትራ ላይ ጥቃት አደረሱ። ከሶስት ወር በኋላ የከረን ጦርነትን በማሸነፍ ሚያዝያ 1941 ሙሉ ኤርትራን ተቆጣጠሩ። የእንግሊዝ ወታደራዊ አገዛዝ() በጣሊያኖች ምትክ አገሪቱን ማስተዳደር ጀመረ። 1947 ጣሊያን በፈረመችው የሰላም ውል መሰረት ኤርትራ ለአራቱ ሃይላት ተሰጠች። ከዚህ በኋላ ኤርትራ የጣሊያን ቅኝ መሆኗ አበቃላት። ሕግና ስርዓት እንግሊዞች የመጀመሪያ አላማቸው ሕግና ስርዓትን ማጽናት እንዲሁም አገሪቱን ማረጋጋት ነበር። ለዚህ ሲሉ ጣሊያኖች ሲሰሩበት የነበረውን ስርዓት ብዙ ሳይቀይሩ ነበር መግዛት የጀመሩት። በ'44 እና '47 መካከል የኤርትራን ግዛቶች በብሔር ከ5 ከፍለው እንደገና አዋቀሩት። ይህ አዲሱ አወቃቀር ከጣሊያኖቹ እምብዛም አይለም ሆኖም ግን ከረንንና አቆርዳትን አንድ በማድረግ "ምዕራባዊ ግዛት" ስያሜ ሰጥተው አዲስ ክፍል አድርገዋል፣ ምፅዋንና አሰብን በማዋሃድ የቀይ ባሕር ክፍል ብለው ሰይመዋል፡ ሁለተኛው የአለም ጦርነት እንግሊዞች ከነበረባቸው የሰው ሃይል ማነስ የተነሳ የጣሊያን ተቀጣሪወችን ሳይቀር የቀደሙትን የአገሬውን ባለስልጣኖች ሳያባርሩ ነበር ግዛታቸውን የጀመሩት። የጣሊያኖችም ህጎች በነበሩበት እንዲጸኑ ተደርገዋል። ሆኖም ግን የአፓርታይድ ስርዓቱን አስቀርተው አገሬው የጤናና የትምህርት፣ የመናገር ነጻነትና የስራ እድል ተቋዳሽ እንዲሆን አድርገዋል። የትምህርት ቤቶች ቁጥር 100 ሲደርስ በዚህ ወቅት ትምህርት በትግርኛእና አረብኛ ይሰጥ ነበር። የሁለተኛው የአለም ጦርነት ካስነሳው የኢኮኖሚ ፍላጎት አንጻር ኤርትራ የእርሻና የኢንደስትሪ ምርቷ በክፍተኛ ደረጃ አደገ። እንግሊዞቹ ወደ 256 ሺህ ሄክታር መሬት በመቆጣጠር 59ሺህ ቶን የሰብል ምርት ለመሰብሰብ ቻሉ። ኢኮኖሚው በዚህ መንገድ ከማደጉ የተነሳ ኤርትራ እርሷን የቻለች ሆነች። የተማሩ ጣሊያኖችና ወዝ አደር የአገሬው ሰወች በእንግሊዞች እየተቀጠሩ ይሰሩ ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ የአገሬው ህዝብ የንግድ ማህበር እንዲያቋቁሙ የተፈቀደው በዚህ ጊዜ ነበር። ከጦርነቱ በኋላ በጦርነቱ ወቅት ኢኮኖሚው ይደግ እንጂ፣ እንግሊዞቹ የበለጠ ትርፍ ለማግኘት ሲሉ ጣሊያኖች የዘረጉትን አብዛኛውን ኢንደስትሪና ኢንፍራስትራክቸር በመነቃቀል ሸጡ። ከአለም ጦርነት በኋላ የኢኮኖሚክ ፍላጎት ማንስ ባስነሳው ሁኔታ የኤርትራ ኢኮኖሚያዊ እድገት ተጨናገፈ። የእግንሊዙ ወታደራዊ አስተዳደር ያስቀመጠው የብድር፣ የላይሰንስ፣ የውጭ ገንዝበና የምርት ገደብ ለአገሪቱ ኢኮኖሚ መጨናገፍ ደጋፊ ነበር። የእርሻና የኢንደስትሪ ውጤቱም ከውጭ ካለው ፉክክር የማይከለከል ስለ ነበር ሌላው የኢኮኖሚው ቁስል ነበር። ይህ ሁሉ ተደማምሮ 1948ዓ.ም. ላይ የአገሪቱ ኢንደስትሪ እንዲዘጋና ወደ 10፣000 የሚጠጋ ኤርትራዊ ስራ አጥ እንዲሆን አደረገ። ኢኮኖሚያዊ ቀውሱና የዕቃወችን ውድነት ተከትሎ ብሔራዊነት ገኖ መውጣት ጀመረ። የአገሪቱ ኤኮኖሚና አስተዳደር በኤርትራውይን እንዲደረግ ጥያቄ መቅረብ ጀመረ። ማህበር ፍቅሪ ሐገር ከ1941 ጀምሮ ሁሉንም ኤርትራውያን ያሳተፈ ፀረ-ቅኝ ግዛት ማህበር -ማህበር ፍቅሪ ሐገር ተቋቁሞ ነበር። የዚህ ማህበር አላማ የህብረተሰቡን ፍላጎት ለእንግሊዞቹ ማስረዳት ነበር። ቀስ ብሎ ግን ከተማ ኗሪው ትግርኛ ተናጋሪ ክፍል ፅንፈኛ፣ ኢትዮጵያን የሚደግፍ አቋም መያዝና ማህበሩን መቆጣጠር ጀመረ። 1943 ላይ አብዛኞቹ እስልምና ተከታዮችና አንድ አንድ የደቡብና መሃከለኛ ደጋማ ክፍል ክርስቲያኖች ማህበሩን ለቀው የመለያየት እንቅስቃሴን ጀመሩ። 1946 ላይ የአንድነት ደጋፊወችና የሱዳን መከላከያ ሃይሎች (በእንግሊዞች ስር የነበሩ) አስመራ ውስጥ ደም ተፋሰሱ። ይህ ሁኔታ የፖለቲካ ውጥረትን ያስከተለና የጣሊያን ኗሪዎች በአንድነት ደጋፊዎች ከዚህ በኋላ ጥቃት እንዲደርስባቸው ያደረገ ነበር። ጥቅምት 1946 ላይ እንግሊዞች በፖለቲካ ፓርቲወች ላይ ያስቀመጡትን ዕቀባ አነሱ። 1947 ላይ ጣሊያኖች በፈረሙት የሰላም ውል መሰረት የኤርትራን የወደፊት ዕድል የተባበሩት ሃይሎች እንዲወስኑ ተደረገ። የተባበሩት ሃይላት የአገሬውን ፍላጎት ለማወቅ አጣሪ ኮሚሽን ላኩ። በዚህ ጊዜ ኤርትሪያ ውስጥ 4 ጉልህ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይንቀሳቀሱ ነበር፣ እነርሱም ፩ - አንድነት ፓርቲ - ኅዳር 1947 ላይ እንደ ፓርቲ እውቅናን ያገኘ ነበር። ይደገፍ የነበረውም በትግርኛ ተናገሪዎቹ የሐማሴን ክፍሎች እና ባላባት እስልምና ተከታዮች ነበር።ይህ ፓርቲ ትልቅ የኢትዮጵያ መንግሥት እጅ ነበረው አቋሙም ያለምንም ድርድር ከኢትዮጵያ ጋር መዋሃድ የሚል ስለነበረ። ይዞታው የአገሪቱን 48% ድጋፍ ያገኘ ከነበሩት ፓርቲዎች ሁሉ ታላቁ ነበር። ፪ - መስሊም ሊግ - ሁለተኛው ታላቁ ፓርቲ ሲሆን 30% የአገሪቱን ድጋፍ ያገኘ ነበር። ከባላባቶች ውጭ የሆኑትን መስሊሞች ድጋፍ ያገኝ ነበር። አቋሙ ኤርትራ ተገንጥላ እራሷን መቻል አለባት፣ ይህ ካልሆነ ተገንጥላ በተባበሩት መንግስታት ትመራ፣ የሚል ነበር። ፫ - ለዘብተኛ ተራማጅ ፓርቲ- ከማህበረ ፍቅሪ አፈንግጠው ተገንጣይነትን ከሚያራምዱት ቡድኖች የመጣ ሲሆን አብዛኛው ደጋፊ ደገኛ ክርስቲያኖች ነበሩ። ይህ ፓርቲ በወታደራዊው አገዛዝ() የሚደገፍ ነበር። አቋሙም ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉትን ትግርኛ ተናጋሪዎች ጨምሮ ከኢትዮጵያ መገንጠል ነበር። ፬ - ጣሊያንን ደጋፊ ፓርቲ - የዚህ ፓርቲ ደጋፊዎች ኗሪ ጣሊያኖች፣ ክልሶችና በቅኝ ግዛቱ ወቅት ጥቅም የነበራቸው ኤርትራውያን ነበሩ። አቋማቸው የጣሊያን ፓለቲካዊ ግዛት በኤርትራ ተመልሶ እንዲቋቋም ነበር። ከዚህ በተረፈ የኢትዮጵያ፣ ታላቋ ብሪታኒያና ጣሊያን የራስ-ፍላጎቶች የኤርትራን የወደፊት እድል ያወሳሰበ ጉዳይ ነበር። የታላቋ ብሪታንያ አቋም ኤርትራ እራሷን መቻል የማትችል አገር ስለሆነች ከሁለት ተከፍላ እስላሞች የሚኖሩበት ምዕራባዊው ክፍል ለሱዳን እንዲሰጥ፣ ክርስቲያን ትግርኛ ተናጋሪው ደጋ ክፍል ለኢትዮጵያ እንዲሆን ነበር። የጣሊያን ፍላጎት በተባበሩት መንግስታት ቡራኬ የኤርትራ ሞግዚት ሆና እንድታስተዳድረው፣ ያ ካልሆነ አገሪቱ ለብቻዋ እንድትሆን ነበር። የኢትዮጵያ አቋም፣ ከታሪክ፣ ከመልክዓምድር፣ ከብሔርና ከኢኮኖሚ አንጻር፣ እንዲሁም ከስትራቴጂክ ፍላጎት አንጻር፣ ማለት የባሕር በር እንዲኖራት አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ኤርትራ የርሷ እንደሆነች ነበር። አጼ ሃይለ ሥላሴ በቅኝ ግዛት ወቅት የተወሰደውን መሬት ለኤርትራውያን አስመልሳለው ብለው ቃል ሲገቡ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ቄሶች ሙሉ በሙሉ ደጋፊያቸው ሆኑ፣ በግልጽም የአንድነት ፓርቲ ደጋፊዎች ሆነው ይሰሩ ነበር። ከ1947-48 የአራቱ ሃይሎች አጣሪ ኮሚሽን ወደ ኤርትራ ሄዶ የህዝቡን ልብ ትርታ ለማጥናት ያደረገው ሙከራ በኮሚሽነሮቹ መካከል ስምምነት ስላልፈጠረ እና የኢትዮጵያ ጣልቃ ገብነትም ለመለየቱ አስቸጋሪ ስለነበረ በ1948 ላይ ጉዳዩ ለአለም አቀፉ የተባበሩት መንግስታት መድረክ ቀረበ። እንግሊዞችና ጣሊያኖች የቤቭን ፎርዛ አቅድ የተባለውን ሰነድ ያዘጋጁት በዚህ ወቅት ነበር። በአቅዱ መሰረት ኤርትራ ከሦስት ስትከፈል ምዕራቡ እስላም ክፍል ለሱዳን፣ ደጋው ለኢትዮጵያ፣ ዓሰብና ምጽዋዕ ልዩ ግዛት እንዲሆኑ ነበር። ሆኖም ግንቦት 1949 ላይ የተካሄደው የተ.መ. ጉባኤ ሃሳቡን ውድቅ አደረገው። ይህን ተከተሎ ኤርትራ ውስጥ ፖለቲካዊ ቀውስ ተነሳ። መስሊም ሊግ የለዘብተኛ ተራማጅ ፓርቲንና የጣሊያን ደጋፊ ፓርቲን ሃይሎች በማስተባበር ታላቅ የተገንጣይ ቡድን መሰረተ። ሆኖም ግን በአባሎቹ የሶሽዮ-ፖለቲካ መሰባጠር ምክንያት ሃይሉ የዳከመ ነበር። በዛ ላይ የጣሊያንን እንደገና መምጣት በመፍራትና የኢትዮጵያን ሙስሊሞችን ለማክበር ቃል መግባት በመከተል ብዙዎች ከኢትዮጵያ ጋር ይህ-ከሆነ ውህደት እንዲፈልጉ አደረገ። የኢኮኖሚው መንኮታኮትም በእስላሞችና ክርስቲያኖች መካካከል እንዲሁም በቋንቋ-ብሔሮች መካከል ውጥረት አስነሳ። መስሊም ሊግ ጭሰኝነትን አስወግዳለሁ በማለቱ የሙስሊም ባላባቶች ውህደትን እንዲደግፉ አደረገ። 1950 ላይ የተ.መ. ሃቅ ፈላጊ ቡድን ኤርትራ በመሄድ ከመጋቢት እስከ ሚያዝያ የህዝቡ ፍላጎት ላይ ጥናት አካሄደ። በዚህ ወቅት ሽፍቶች በመገንጠል ደጋፊዎች ላይ ከፍተኛ ጥቃት አደረሱ። የሃቅ ፈላጊው ቡድን አባል የሆኑት የኖርዌይ ተወካይ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር አንድ እንድትሆን፣ የበርማና ደቡብ አፍሪቃ በፌዴሬሽን እንድትዋሃድ፣ የፓኪስታንና ጓቴማላ ተወካዮች ለ10 አመት በተ.መ. ሞግዚትነት ተዳዳራ በኋላ እራሷን እንድትች ሃሳብ አቀረቡ። ሁሉም አባላት ኤርትራ ወዲያውኑ እራሷን እንደማትችል፣ ለዚህ ምክንያቱ የሶሺዮ-ኢኮኖምክ ብቃት አለመኖርን። ከብዙ ክርክርና የዲፕሎማሲ ፍትጊያ በኋላ፣ ታህሳስ 1950 ላይ የተ.መ. አጠቃላይ ጉባኤ ) ላይ የእጅ ምርጫ በማድረግ አጸደቀ። በጸደቀው ድንጋጌ መሰረት ኤርትራ በፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ጋር እንድትቀጥል።ፌደረሽኑም የሁለቱም አገሮች እኩል መብት ኑሯቸው የፌደሬሽን ባንዴራ ኑሯቸው እንዲቀጥሉ ነበረ፤ ."ወደ አማርኛ ሲገለበጥ ፤የተ.መ የኤርትራን ፍላጎት ሳይሰማ ከኢትዮጵያ ጋር አቆራኛት፤የዚያን ጊዜ አምባሳደር ጆን ፎስተር ዳላስ በኋላ ዋና ጸሓፊ የሆኑት እንዳሉት «ከህግ አንጻር የኤርትራን ህዝብ ፍላጎት መሰማት ነበረበት ሆኖ ግን የኛ የተ.መ ስትራቴጂ በቀይባህር ያለንን አንጻር እና የአለም ሴኩሪቲን ለማስጠበቅ ከጓደኛችን ኢትዮጵያ እንድትቀላቀል አድርገናል» አሉ፤ .ከሁለት አመት የሽግግር መንግስት በኋላ ፌዴሬሽኑ መስከረም 1952 ላይ ተግባር ላይ ዋለ። ኢትዮጵያ ኤርትራ ፌዴሬሽን የፌዴሬሽን አስተዳደር ለአካባቢው እንግዳ ስለነበር የተለያዩ ክፍሎች በተለያየ መልኩ እንዲተረጉሙት ሆነ። የኢትዮጵያ መንግስት ፌዴሬሽን ማለቱ ኤርትራን ወደ ኢትዮጵያ የሚያጠቃልል ነው ብሎ ተረጎመ። በኤርትራ በኩል፣ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ፌዴሬሽኑን ቢቀበሉም በአተረጓጎሙ ላይ ልዩነት አሳዩ። አንድነት አራማጆች ትርጉሙን ኢትዮጵያ በምታይበት አይን ሲመለከቱ በኢብራሂም ሱልጣን የሚመራው የኤርትራ ዲሞክራሲያዊ ግንባር የመገንጠል ደጋፊዎችን በማነሳሳት የኤርትራን ራስ ገዝነት አጉልቶ በሚያሳይ መልኩ ይተረጉሙ ነበር። በተ.መ. የፌዴሬሽኑ ድንጋጌ መሠረት የሁለቱን ክፍሎች ግንኙነት የሚያስተዳድሩ ልዩ ተቋማት እንዲፈጠሩ አልተደረገም። ነገር ግን በምክር ለመርዳት ያክል የተባለ ተቋም ተበጅቶ የነበር ሲሆን በቂ ኃይል ግን አልነበረውም ። ስለዚህ እውነተኛው የፌዴራሉ መንግስት የኢትዮጵያ መንግስት ነበር። በሽግግሩ ወቅት የእንግሊዙ ወታደራዊ አስተዳደር የኤርትራን ህገ መንግስት እንዲህ ሲል ቀረጸ፣ ኤርትራ ራሱን የቻለ ግዛት ሲሆን ኤርትራዊ ዜግነትን ፣ ብሔራዊ ቋንቋን (ትግርኛና አረብኛ)፣ የተለየ ሠንደቅ አላማን፣ ማህተምንና ልዩ መንግስትን ለኤርትራ ይሰጣል። በራሱ ጉዳይ ዙሪያ ህግ ማጽደቅ ፣ ህግ ማስፈጸምና ፍርድ መፍረድ እንዲችል ለኤርትራው መንግስት ይፈቅዳል። የአካባቢውን ሥነ ንዋይ መቅረጽ፣ ግብር መሰብሰብ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ መስተዳድር እና የፖሊስ ስራ በዚሁ በኤርትራው መንግስት ስር ይከወናሉ። የፖለቲካ ፓርቲወች፣ የንግድ ማህበራት፣ የሰው ልጅ መብቶች፣ የህትመትና የመናገር ነጻነትንም ይፈቅዳል። የፌዴራሉ መንግስት በአንጻሩ የውጭ ጉዳይን፣ መከላከያን፣ ገንዘብን፣ ፋይናንስን፣ የውጭ ንግድና የኢትዮጵያና ኤርትራን ንግድን፣ መገናኛን በተመለከተ ስልጣን ይኖረዋል። በተጨማሪ የፌዴራል መንግስቱን ስራ ለማካሄድ አንድ አይነት ግብር እንዲያወጣ ይገደድ ነበር። በዚህ ወቅት አቶ አንዳርጋቸው መሳይ (የአጼ ኃይለ ስላሴ አማች) በኤርትራ የኢትዮጵያ መንግስት ተወካይ ነበሩ። የኤርትራ ምክር ቤት የኤርትራ ምክር ቤት (ባይቶ ኤርትራ) በእንግሊዞች አቀናባሪነትና አገር አቀፍ ምርጫ መጋቢት 1952ዓ.ም. ሲመሰረት በዚሁ ወቅት የኤርትራን ህገ መንግስትና የፌደሬሽኑን ደንብ አጸደቀ። እንዲሁም አቶ ተድላይ ባይሩን እንደ ዋና ስራ አስፈጻሚ ና አቶ አሊ አህመድ ሙሳ ረዳይን እንደ ፕሬዜዳንት አድርጎ መረጠ። በዚያው አመት መስከረም ላይ የኢትዮጵያም መንግስት እንዲሁ ሁለቱን አጸደቀ። መስከረም 15 ላይ የአስተዳደሩ ሃይል ወደ ፌዴራል መንግስት ተዛወረ። ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያውም ሆነ የኤርትራው ውገኖች ለራሳቸው በሚስማማ መልኩ የፈዴሬሽኑን ደንቦች በመተርጎም ቀስ በቀስ የፖለቲካ ውጥረት ተነሳ። የአንድነት ደጋፊ የነበሩት አቶ ተድላ ባይሩ 1953 ላይ የፖለቲካ ተቃውሚዎቻቸው ወልደ አብ ወልደ ማርያምንና አብርሃ ተሰማን በመወንጀል ጥቃት ጀመሩ። የአንድነት ፓርቲ አቶ ተድላ ባይሩን በመደገፍ ኤርትራን ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ ጋር ማዋሃድ አላማው አድርጎ ተነሳ። እኒህ የአንድነት ደጋፊዎች በመንግስት ቢሮዎች ለየት ያለ ስራ የማግኘት እድል ስላገኙ የተገንጣይ ሃይሎች (የኤርትራ ዲሞክራሲያዊ ግንባር) እጅግ ተበሳጩ። በተለይ በእስላማዊው ምዕራብ ኤርትራ ግንባሩ ከፍተኛ ድጋፍን ማግኘት ጀመረ። የኢኮኖሚው እየወደቀ መሄድ፣ የግብር መጨመርና የቁሳቁሶች ዋጋ መጨመር ለውጥረቱ መባባስ አስተዋጽኦ አደረጉ። በዚህ ወቅት ኤርትራ የምታስገባውና የምታስወጣው ዕቃ ላይ 25% የግብር ጭማሪ ተደርጎ ነበር። የጣሊያን ዜጎችም በጦርነቱ ያጡትን የኢንደስትሪ፣ ማዕድን ማውጣት፣ እርሻ ወዘት መብቶች ከእንደገና በማግኘታቸው አገሬው ህዝብ እንዲበሳጭ ካደረጉት ጉዳዮች አንዱ ነበር። በዚያው አመት በ1953 ሙስሊም ሊግ መነሳሳትን አሳየ። እንዲያውም የእስላምናን ፍላጎትና የኤርትራን ህገ መንግስት እንደግፋለን በማለት ህዝባዊ አመጽ ማደራጀት ጀመረ። የኤርትራው ሥራ አስፈጻሚ ሊቀመንበር የህትመት ነጻነትን በመንፈግ አመጹን ለማፈን ሞከረ። 1954 ላይ ሙስሊም ሊግ በበኩሉ ለአጼ ሃይለ ስላሴ እና ለተባበሩት መንግስታት የመብቱን መታፈን በመቃወም ደብዳቤ ጻፈ። ነገር ግን ተቃውሞው አንድ ወጥ አልነበረም። በሙስሊም ሊግ ውስጥ በተነሳ ውስጣዊ ቅራኔ ኢብራሂም ሱልጣን ከሊጉ ተባረረ። የሆኖ ሆኖ ሙስሊም ሊግ በኤርትራ ምክር ቤት ባደረገው ዘመቻ አቶ ተድላ ባይሩ ምክር ቤቱ ክብር እንዲያጣና በራሱ ፓርቲ እንዲወቀስ አድርገው ነበር። በኤርትራው ምክርቤትና በሥራ አስፈጻሚው ሊቀመንበር (ፕሬዘዳንት አሊ ረዳይ)ውጥረት የተጀመረው በዚህ ወቅት ነበር። ምክር ቤቱ ተድላ ባይሩን ከመጥላቱ የተነሳ እርሱን ከስልጣን ለማባረር አሊ ረዳን ማባረር ግድ እንዲላቸው ስለተረዱ ሴራ ማሴር ጀመሩ። ተድላ ባይሩ በበኩሉ ህገ መንግስቱ ከሚፈቅደው ጊዜ በላይ፣ ምክር ቤቱ እንዲዘጋ (ሰስፔንድ እንዲደረግ) አደረገ። የተቃዋሚው ሃይል እሮሮውን ወደቀዳማዊ አጼ ሃይለ ስላሴ በማሰማት ጣልቃ እንዲገቡ አደረገ። ንጉሱም የነገሩን ኢ-ህገ መንግስታዊነት በመመልከት አቶ ተድላ ባይሩና ፕሬዜዳንት አሊ ረዳይ ከስልጣናቸው እንዲለቁ አደረጉ። በዚህ ወቅት ቢትወደድ አስፍሐ ወልደሚካኤል ተድላ ባይሩን ተክቶ ተሾመ። አስፍሐ ወልደሚካኤል የአንድነት ፓርቲ ደጋፊ ነበሩ። ምክር ቤቱ በተራው ሼክ ሳይድ እድሪስ ሙሃመድ አዲምን (የኤርትራ ዲሞክራሲ ግንባር ተወካይ) ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ። ከዚህ በኋላ በአንድነት ፓርቲና በሙስሊም ሊግ መካከል ብዙ መቆራቆስና በኋላም የሙስሊም ሊግ ከሁለት መከፍል ተፈጸመ። መስከረም 1956 ላይ በተደረገ የምክር ቤት ምርጫ ከ68 መቀመጫወች 32ቱን የአንድነት ፓርቲ አሸንፎ በጠንካራነት ወጣ። ከሁለተኛው የአለም ጦርነት መጨረሻ ጀመሮ በተነሳው የኢኮኖሚ ማሽቆልቆል ሽፍቶች በአገሪቱ መከሰት ጀመሩ። ህዳር 1956 ላይ አጼ ሃይለ ስላሴ ለምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር ኤርትራን ወደ እናት ሃገሯ ኢትዮጵያ የመመልስ ጉዳይ አንስተው ነበር። በጊዜው የአረብ አብዮት በአካባቢው እየተስፋፋ ስለነበር ለኤርትራም አስጊ ሁኔታ የፈጠረበት አጋጣሚ ነበር። ጥቅምት 1957፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያምና ኡመር ቃዲ ለተባበሩት መንግስታት በጻፉት ደብዳቤ የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስታት በሚያሴሩት ሴራ የፌዴራል ደንቡ እየተሸረሸረ እንደሆነ አስገነዘቡ። የፌዴራል ባለስልጣኖች ኡመር ቃዲን በማሰር አንድ አንድ የተነሱ ሰላማዊ ሰልፎችንና አድማዎችን በማፈን ሁኔታውን አለዘቡት። 1958 ላይ የኤርትሪያ ሥራ አስፈጻሚ ፕሬዘዳንት የኢትዮጵያን የቅጣት ህግ፣ ሰንደቅ አላማና ግብር ስርዓት በኤርትራ ላይ አጸና። ብርጋዴር ጄኔራል አብይ አበበ በዚህ ወቅት የንጉሱ ተወካይ በኤርትራ ሆነው ተሹመው ነበር። በዚህ ትይዩ ሶስት የፖለቲካ ሃይሎች በግብፅ ተደራጅተው ነበር፣ እነርሱም የኤርትራ ነጻነት እንቅስቃሴ - በወልደ አብ ወልደ ማርያም የሚመራ፣ የኤርትራ ነጻነት ግንባር (ጀብሃ) - በእድሪስ ሙሃመድ አዲም የሚመራ፣ የኤርትራ ዲሞክራቲክ ግንባር አንድነት ፓርቲ- በኢብራሂም ሱልጣን የሚመሩ ነበሩ። መጀመሪያ እኒህ ሃይሎች የተባበሩት መንግስታትን ትኩረት ለመሳብ ቢጥሩም ስላልተሳካላቸው በአረብ አገሮችና በሶማሊያ እርዳት ወደ ትጥቅ ትግል ገቡ። ግንቦት 1960 ላይ ምክር ቤቱ የኤርትራ አስተዳደር፣ በኢትዮጵያ ንጉስ ሃይለ ስላሴ ስር የሚለውን ስያሜ ለኤርትራ መንግስት መረጠ። ነገር ግን የኢኮኖሚው አለመረጋጋት በሰራተኛው መደብ ውስጥ አድማና ተቃውሞ አስነሳ። ይህ የኢኮኖሚ ቀውስ ኢ-ኢትዮጵያዊ ቅርጽ ነበረው። 1961 ላይ እድሪስ አዋተና ጥቂት ተከታዮቹ በስሜን ምዕራብ ኤርትራ የትጥቅ ትግል አስነሳ። ግንቦት 1962 ተማሪዎች የኤርትራ ነጻነትን በመደገፍ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ እንዲሁም በዚሁ ውቅት ኢ-ኢትዮጵያዊ ሴራ በአገሪቱ ውስጥ ተደርሶበት ከሸፈ። ሐምሌ 1962 ላይ ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ ሁኔታውን ለማረጋጋት ወደ ኤርትራ ተጉዘው ነገሮች ሊረግቡ ቻሉ። ከአምስት ወር በኋላ ህዳር15፣ 1962 የኤርትራ ምክር ቤት ባደረገው ምርጫ ፌዴሬሽኑ እንዲፈርስና ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር እንድትቀላቀል ወሰነ። ምርጫውን ተከትሎ አጼ ሃይለስላሴ የፌዴራሉን ደንብ ውድቅ በማድረግ ኤርትራ የኢትዮጵያ 14ኛ ጠቅላይ ግዛት አደረጉ። የኢትዮጵያ ክፍለ ሐገር ኤርትራ የኢትዮጵያ ክፍለ ሐገር ከሆነች በኋላ ያለው ጊዜ በሁለት ጉልህ ዘመናት ይከፈላል፣ እነርሱም የዘውዱ ጊዜና የደርግ ዘመናት ናቸው። የዘውድ ዘመናት በዘውዱ አገዛዝ ወቅት ከኢትዮጵያ ወገን አንድ ወጥ ሳይሆን ያመነታ ሁለት አይነት አቋም ታይቷል፡ የመጀመሪያው አቋም በጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ ይመራ የነበር ሲሆን አቋሙም ሙሉ በሙሉ ኤርትራን ወደ ኢትዮጵያው ስርዓት ማምጣትና ማዕከላዊነትን ማስፋፋት ነበር። ሁለተኛው አቋም ኤርትራን ከ1964-70 ያስተዳድሩ በነበሩት ራስ አስራተ ካሳ የሚመራ ሆኖ የኤርትራን ማንነት በማይነካ መልኩ፣ ግትር ያለ አቋም ሳይይዝ፣ መንግስት አስተዳደሩን እየለዋወጠ በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲተዳደር ማድረግ ነበር። ለአስራተ ካሳ አቋም መነሻ በክርስቲያን ኤርትራውያን ላይ የነበረው እምነት ነበር። ስለሆነም ኤርትራ የበለጠ ነጻነት ቢሰጣት አገሪቱ ጸንታ ትቆማለች የሚል ነበር። ከኤርትራኖችም አንጻር ሁለት መንታ አቋም ነበር። በተለይ ራስ አስራተ ካሳ የኤርትራ አስተዳዳሪ በነበሩበት ወቅት የተማረው ክርስቲያኑ የኤርትራ ክፍል ከሞላ ጎደል የኢትዮጵያ ደጋፊ ነበር። ብዙ የኤርትራ ክርስቲያኖች ወደ አዲስ አበባ በመሄድ በሃብት የበለጸጉ ኤርትራውያንን መቀላቀል ቀጠሉ። በቁጥር ጥቂት የማይባሉ ኤርትራውያን በዘውዱ ሥርዓት ውስጥ የመሪነት ቦታን አገኙ። በአንጻሩ ያልተማረው ወጣቱ ክፍልና፣ በእንግሊዙ ወታደራዊ አስተዳደር ስልጣን የነበረው ይህን አይነት ኢትዮጵያዊነት ሊቀበል አልቻለም። አብዛኛው የሙስሊም ክፍልም እንዲሁ አልተቀበለም። መላው አረባዊነት እና ጀብሃ ብዙ የምዕራብ ኤርትራና የምጽዋ አካባቢ ሙስሊም ወጣቶች ጀብሃን (የኤርትራ ነጻነት ግንባር)ን መቀላቀል ጀመሩ። ጀብሃ በ1960ዓ.ም ካይሮ ውስጥ የተመሰረተ ግንባር ነበር። እኒህ ሙስሊሞች በጊዜው በካባቢው ተንሰራፍቶ የነበረውን መላው አረባዊነት በመዋስ የኤርትራ ህዝብ አረባዊነትን እንደ መፈክር አነገቡ። በዚያውም በአረብ አገሮች ይካሄድ የነበረውን የትጥቅ ትግል ስልት በጥቅም ላይ ማዋል ጀመሩ። የናስሪዝም እና የባቲዝም ንቅናቄዎችን ከመካከለኛው ምስራቅ በመዋስ ገንዘባቸው አደረጉ። የጀብሃ መፈረካከስና የኤርትራ ህዝብ ነጻነት ግንባር በ60ዎቹ መጨረሻ፣ ምንም እንኳ ጀብሃ እድገት ቢያሳይም የመላው-አረባዊነት አቋሙን በመጥላት አንጎራጓሪ ክርስቲያን ወጣት ኤርትራውያን ሊደግፉት አልቻሉም። ጠረፍ ነዋሪ ሙስሊሞች ጀብሃ በምዕራብ ሙስሊሞች የተሞላና እኛን የረሳ ነው በማለት ለመደገፍ አልፈለጉም። የመላው-አረባዊነት መፈክርም በአረብ አገሮች በተነሳ የርስ በርስ ሽኩቻ ተነኳኮተ። ከዚህ በተጨማሪ ጀብሃ ከሁለት ተከፍሎ በክርስቲያኖች አውራነት የተመሰረት -- የኤርትራ ህዝብ ነጻነት ግንባር (ሻዕቢያ) ሲቋቋም የኤርትራው ትግል ያበቃለት መሰለ ። ሆኖም ግን በጠቅላይ ግዛቱ የሚካሄደው ጦርነት የራስ አስራተ ካሳ አቋም የማይሰራ ስላስመሰለ ህዳር 1970 ላይ ራስ አስራተ ካሳ ከኤርትራ ስልጣናቸው እንዲነሱ ሆነ። ከዚህ በኋላ ወታደሮች በወታደራዊ ስልት ችግሩን እንዲፈቱ ነጻነት ተሰጣቸው። የደርግ ዘመናት ከኢትዮጵያ አብዮት መፈንዳት በኋላ የተነሳው ደርግም እንዲሁ ፖሊሲው ያመነታ ነበር። የደርግ የመጀመሪያው ሊቀመንበር የነበረው የኤርትራው ተወላጅ ጄኔራል አማን አንዶምአገሪቱ በኤርትራ ላይ ትከተል የነበረውን ፖሊሲ ለመገምገም ሞክሯል። በእርሱ ፖሊሲ መሰረት ኤርትራ በኢትዮጵያ ስር ሆና ነገር ግን የራሷ የፖለቲካ ማንነት እንዲኖራት የሚፈቅድ ነበር። አማን አንዶም ከተገደለ በኋላ የርሱ ፖሊሲ ተቀይሮ እስከ 1991 ድረስ የሚሰራበት ፖሊሲ በኮሌኔል መንግስቱ ሃይለማርያምአማካይነት ተፈጻሚነትን አገኘ። ይህ አዲሱ ፖሊሲ በኤርትራ እንቅስቃሴዎች ላይ ወታደራዊ ድልን በመቀዳጀት ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህ ሁኔታ፣ አብቅቶለታል ተብሎ የነበረው የኤርትራ አመጽ ማንሰራራት ጀመረ። በ1970ዎቹ ሁለተኛ አጋማሽ ላይ ሻዕቢያ ሙሉ ጥቃትን ማድረስ ጀመረ። ምንም እንኳ ሁሉም ግንባሮች የኢትዮጵያን ሰራዊት የሚታገሉ የነበሩ ቢሆንም፣ ኤርትራውያን አንድ መሆን አልቻሉም ነበር። በተለይ ማርክሲስት የነበረው ሻዕቢያ ብዙ ክርስቲያን ኤርትራውያን ሲቀላቀሉት፣ ኃይሉ ከማደጉ የተነሳ፣ በመላው አረባዊነት አራማጁ ጅብሃ ላይ ጦርነት መክፈት ጀመረ። ከ1981-84 በተደረገ እርስ በርስ ጥሮነት ሻዕብያ የበላይነቱን ተጎንጻፎ ብቅ አለ። ከ80ዎቹ አጋማሽ ጀመሮ ኢትዮጵያ ውስጥ ይካሄድ የነበረው ጥርነት እየተጠናከረ ሲሄድ ሻዕቢያ ወሳኝ ድሎችን ማስመዝገብ ጀመረ። 1987 ላይ ሶቭየት ህብረት ለደርግ የሚያደርገውን እርዳታ ሲያቋርጥ ሁኔታዎች ለሻዕቢያ ተመቻቹ። መጋቢት 1988 የአፋቤት ጦርነት ተብሎ በሚታውቀው የሻዕቢያ ሰራዊት በደርግ ሰራዊት ላይ ስልታዊ የሆነ ድል ተቀዳጀ። ከዚህ በኋላ የአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ ስልጣን እየገነነ ግንባሩም ድል እየተጎናጸፈ ሄዶ ግንቦት 1991፣ በኢትዮጵያ የደርግ መውደቅን ተከትሎ ኤርትራ ኢ-ጥገኝነቷን ለማግኘት ቻለች። የኤርትራ ትግል በኢትዮጵያ ላይ ብዙ አሻራ የተወ ሲሆን በተለይ የነጻነት ግንባር ጽንሰ ሃሳብን ከአረብ አገሮች በማስመጣት በአካባቢው ማስፋፋቱ ተጠቃሽነት አለው። ሃገረ ኤርትራ (ከ1991 በኋላ) አጠቃላይ የአገሪቱ ሁናቴ፣ በተለይ የውጭ ግንኙነት ኤርትራ እራሷን ከቻለች በኋላ ለተወሰነ ጊዜ የኢኮኖሚ እድገትን አሳይታለች። ሆኖም ግን ከጎረቤቶቿ ጋር የሰላም ግንኙነት አልነበራትም። ከሱዳንጋር እርስ በርስ በመወነጃጀል በ1990ወቹ የፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ገብተው ነበር። 1995 እና 96 ደግሞ ከየመን ጋር በሐኒሽ ደሴቶች ዙሪያ ጦርነት አድርጋ 1998 ላይ በተ.መ. ውሳኔ መሰረት ደሴቶቹ ለየመን ተሰጡ። ከዚህ በኋላ ቀዝቀዝ ያለ ሰላም በሁለቱ መካከል ሰፈነ። ከኢትዮጵያ ጋር የነበራት ግንኙነት መጀመሪያ የወዳጅነት ቢሆንም በኋላ ላይ በንግድና በባህር ወደብ አቅርቦት ዙሪያ በተነሱ ጥያቄዎች ውጥረት ገጠመ። 1998ዓ.ም. ላይ ባድሜ በተባለች የጠረፍ መንደር ዙርያ በተነሳ የድንበር ግጭት ውጥረቱ ገንፍሎ ወጥቶ ወደ ጦርነት አመራ። ከሁለት አመት ጦርነት በኋላ ታህሳስ 2000 ላይ የተ.መ. ሰላም አስከባሪ ሃይል በኢትዮጵያ-ኤርትራ ድንበር ላይ ተሰማራ። የአለም አቀፉ የድንበር ኮሚሽን ድንበሩን ለማካለል የወሰደው ውሳኔ በኤርትራ ተቀባይነት ሲያገኝ በኢትዮጵያ ዘንድ በመሪህ ደረጃ ተቀባይነትን አግኝቶ ነገር ግን በተግባር ደረጃ የቤተሰቦችንን መለያየት ይፈጥራል በሚልና ሌሎች ምክንያቶች ተቀባይነት አላገኘም። ኤርትራ በበኩሏ የተ.መ. የሰላም አስከባሪው ክፍል በስለላ ስራ የተሰማራ ነው በማለትና ጫና በመፍጠር 2008 ዓ.ም. ኤርትራን ለቆ እንዲሄድ አደረገች። በዚያው አመት ኤርትራ ወታደሮቿን በራስ ዱሜራ አካባቢ በብዛት ስታሰማራ ከጅቡቲ ጋር የድንበር ጥል ገባች። ይህን ተከትሎ በተነሳ ጦርነት ወደ 30 ሰዎች ሞቱ። ፖለቲካዊ አደረጃጀት፣ በተለይ የአገር ውስጥ አደረጃጀት ከግንቦት 1991 በኋላ ኤርትራ ትመራ የነበረው በጊዜያዊ መንግስት ሲሆን መሪዎቹም የቀደሙት የሻዕቢያ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ነበሩ። የኤርትራምርጫ(ሚያዚያ 23-25) ከተደረገ በኋላ ግንቦት19,1993 ይሄው ጊዜያዊ አካል የኤርትራ ሽግግር መንግስት መሆኑን አወጀ። አላማውም አዲስ ህገ መንግስት እስኪጸድቅና ምርጫ እስኪካሄድ አገሪቱን ለ4 አመት ማስተዳደር ነበር። ከ5 ቀን በኋላ ኢ-ጥገኛ ኤርትራ ግንቦት 24,1993 ላይ በኦፊሴል ታወጀ። የሽግግሩ መንግስት ህግ አርቃቂ አካል (ሀገራዊ ባይቶ) 30 የሻዕቢያ ማዕከላዊ አካላትን እና 60 አዳዲስ አባላትን የያዘ ነበር። 1993 ላይ ይሄው አካል የኤርትራን የመጀመሪያ ፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን መረጠ። ፕሬዜደንቱ የአገሪቱና የመንግስቱ የበላይ አካል ሲሆን በህግ አርቃቂው ኮሚቴ እና በአገሪቱ ምክር ቤት ላይ ሙሉ ስልጣን አለው። በተጨማሪ አቶ ኢሳያስ የሰራዊቱ መሪ እና የሻዕቢያ ዋና ሃላፊ በመሆን ሃይላቸው የገነነ ነው። ከ1994 ጀምሮ ሻዕቢያ ስሙን ቀይሮ ህዝባዊ ግንባር ለፍትሕና ለዲሞክራሲ ተባለ። ግንቦት 1997 የተጠበቀው ኤርትራዊ ህገ መንግስት በጉባኤ ቢጸድቅም ተፈጻሚነት አጣ። የፓርላማ እና የፕሬዜደንት ምርጫም እንዲሁ ሳይደረግ ቀረ። 150 አባላት ያሉት የአሁኑ ሀገራዊ ባይቶ ይቀደመውን ኮሚቴ 1997 ላይ የተካ ሲሆን 75 የ ሹሞችና እና ተጨማሪ 75 የተመረጡ አባላትን አጠቃሎ ይዟል። የአስተዳደር ክፍሎች በአሁኑ ወቅት ኤርትራ በ6 ዞባዎች ይከፈላል። እኒህ በተራቸው በንዑስ ዞባዎች ይከፈላሉ። የዞባወቹ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ በአገሩ የውሃ አቅርቦት ጠባይ ላይ የተመሰረተ ሲሆን የኤርትራ መንግስት ይህን ያደረገበት ምክንያቱን ሲገልጽ እያንዳንዱ አስተዳደር በራሱ የእርሻ አቅም ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲኖረው እና ታሪካዊ አውራጃዊ ርስበርስ ግጭቶችን በዚያው ለማስወገድ ነው። ዞባዎቹ እና የዞባዎቹ ክፍሎች እኒህ ናቸው: የሕዝብ ስብጥር ታዋቂ ኤርትራውያን ኣቶ ወልደአብ ወልደማሪያም፥ ዓብደል ቃድር ከቢረ ራስ ወልደሚካኤል ፣ ሓሚድ እድሪስ ዓዋተ ፣ እብራሂም ሱልጣን፣ ባሕታ ሓጎስ፣ ተድላ ባይሩ፣ አማን አንዶም ኢሳያስ አፈወርቂ ስብሓት ኤፍሬም ሃይለ ወልደትንሳኤ (ድሩዕ) ጴጥሮስ ሰለሙን ማሕሙድ ኣሕመድ ሸሪፎ ብርሃነ ገብረእግዚኣብሄር በራኺ ገብረስላሴ ጀርማኖ ናቲ ዑቕበ ኣብርሃ ሳልሕ ኬክያ እስቲፋኖስ ስዩም መስፍን ሓጎስ የማነ ገብረሚካኤል (ባርያ) ኣብራሃም ኣፈወርቂ ተኸስተ ሰለሙን ዮሃንስ ትኳቦ ኪሮስ ኣስፋሃ የማነ ተኸስተ ደሳለኝ ነጋሽ ዮናስ ዘካርያስ ስብሓት ኣስመሮም ሳምሶን ሰለሙን ቢንያም ያሬድ ቢንያም በርሀ ምሥራቅ አፍሪቃ
39122
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A5%E1%88%8B%E1%89%B3%20%E1%8A%A0%E1%8B%A8%E1%88%88%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%AC
ብላታ አየለ ገብሬ
ብላታ አየለ ገብሬ (፲፰፻፹፯ ዓ/ም - ታኅሣሥ ፯ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም) የውጭ ጉዳይ አደራዳሪ ()፤ የውጭ ዜጎች ልዩ ፍርድ-ቤት ሰብሳቢ፤ የፍርድ ሚኒስቴር፤ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት እንደራሴ፤ የዘውድ አማካሪ ሆነው የሠሩ ሲሆን የታኅሣሥ ግርግር ጊዜ ከሌሎች መሳፍንት እና መኳንንት ጋር ተይዘው ተገድለዋል። ብላታ አየለ ከአማርኛ በስተቀር፤ ፈረንሳይኛ፤ እንግሊዝኛ፣ ጣልያንኛ እና አረብኛ ጠንቅቀው ያውቁ ነበር። ወላጆቻቸው የጎንደር ተወላጆች ሲሆኑ፣ አባታቸው አቶ ገብሬ አንዳርጋቸው፣ እናታቸው ደግሞ ወይዘሮ ደብሪቱ ቢሰውር ይባሉ ነበር። ብላታ አየለ የተወለዱት በሐረርጌጠቅላይ ግዛት፣ ጋራ-ሙለታ አውራጃ፣ ግራዋ የተባለ ሥፍራ ላይ እንደነበረና የተወለዱትም በ፲፰፻፹፯ ወይም ፲፰፻፹፰ ዓመተ ምሕረት እንደነበር ተዘግቧል። መሠረተ ትምሕርታቸውንም የተከታተሉት እዚያው ሐረር ውስጥ በሚሲይናውያን ትምህርት ቤት ነበር። ከጠላት ወረራ በፊት አበራ ጀምበሬ እና ሺፈራው በቀለ (፲፱፻፺፭ ዓ/ም) ባዘጋጁት አጭር የሕይወት ታሪክ ላይ እንደተዘገበው፣ ብላታ አየለ በሐረሩ የካቶሊክ ሚሲይናውያን ትምህርት ቤት ሳሉ በድሬዳዋ ፖስታ ቤት ተቀጥረው ለስድስት ዓመታት እንዳገለገሉና በ፲፱፻፲ ዓ/ም ከወይዘሮ ማርታ ንዋይ ጋር እንደተጋቡ እንረዳለን። ወዲያውም ወደ ድሬዳዋ የጉምሩክ መሥሪያ ቤት ሹም ሆነው ከተዘዋወሩ በኋላ የመሥሪያ ቤቱ ሥራ አስኪያጅነትን ተሹመው እስከ ፲፱፻፳ ዓ/ም አገለገሉ። በ፲፱፻፳ ዓ/ም፣ በወቅቱ የአዲስ አበባ ጉምሩክ ኃላፊ የነበሩት አቶ ገብረ እግዚአብሔር ፍራንስዋ ወደ አውሮፓ በመላካቸው አየለ ገብሬ በጊዜያዊ አስተዳዳሪነት ተሹመው ወደ ርዕሰ-ከተማዋ አመሩ። አቶ ገብረ እግዚአብሔርም የሐረሩ ሚሲዮን ምሩቅ ሲሆኑ፤ ከዚሁ ከአውሮፓ ጉዟቸው ሲመለሱ ነጋድራስ (በኋላ ራስ ቢትወደድ) መኮንን እንዳልካቸውን ተክተው ጊዜያዊ የንግድ ሚኒስትር ሆነው ተሹመው ሳሉ በሙስና ተከሰው የገንዘብ እና የሦስት ዓመት እሥራት ተቀጥተዋል። ብላታ አየለ ገብሬ ግን ለአንድ ዓመት በአዲስ አበባ የጉምሩክ ኃላፊነት ከሠሩ በኋላ በመጋቢት ወር ፲፱፻፳፩ ዓ/ም በከንቲባ ነሲቡ ዘአማኔል ሥር የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ሆነው ለሦስት ዓመታት ሠርተዋል። በ፲፱፻፳፬ ዓ/ም የውጭ ዜጎች ልዩ ፍርድ-ቤት ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ። ይህ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያውያን እና በውጭ ዜጎች መኻል ብቻ በሚከሰቱ ወንጀሎችና ቅራኔዎች ላይ ፍትህ ለመስጠት የተመሠረተ ልዩ ፍርድ ቤት ሲሆን ከዳኞቹ መኻል የውጭ ዜጋውን ቆንስላ ወይም ሌጋሲዮን የወከለ የአገሩ ዜጋ አብሮ ይመደብበት ነበር። ጉዳዩ የሚመለከታቸው፤ ከሳሽም ተከሳሽም የውጭ ዜጎች የሆኑ እንደሆነ ግን በፍርድ የሚቀመጡት ዳኞች ሙሉ በሙሉ የአገራቸው ወኪሎች ሲሆኑ የፍትሁም መሠረት በአገራቸው ሕግ እንጂ የኢትዮጵያን ሕግ አይመለከትም ነበር። በኢጣልያ ወረራ ዘመናት ግፈኛው የፋሺስት ኢጣልያ መንግሥት ኢትዮጵያን እንደወረረ ብላታ አየለ ገብሬ ታማኝነታቸውን ለዚሁ ወራሪ ኃይል መስክረው ከገቡለት የመጀመሪያዎቹ ኢትዮጵያውያን አንዱ ነበሩ። ከጣሊያኖቹም ጋር በመተባበር የፍርድ ሥራውን በማቀነባበር የሠሩ ሲሆን የካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በግራዚያኒ ላይ የደረሰውን የቦምብ አደጋ ተከትሎ፣ ጥፋተኛ የተባሉትን ኢትዮጵያውያን በማደን ተባብረዋል። ከዚህም አልፎ፤ በማንኛውም አገር-ወዳድ እና የታሪኩን ዘገባ በተረዳ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ዘላቂ ቁስልን ያሳደረው ድርጊታቸው በሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ላይ የሞት ፍርድ ቅጣት የመሐል ዳኛው ኢጣሊያዊው ኮንቴ ዴላ ፓርቶ ጋር ግራና ቀኝ ከተቀመጡት ሁለት የኢትዮጵያ ተወላጆች አንደኛው መሆናቸው ነው። የግራ ዳኛውን ወንበር የያዙት ሁለተኛው የኢትዮጵያ ተወላጅ እና የክፍሌ ወዳጆ አባት የነበሩት ነጋድራስ ወዳጆ ዓሊ ናቸው። ይህም ሆኖ ብላታ አየለ በኢጣልያ ሹማምንቶች ግንዛቤ ታማኝነታቸው ጥርጣሬ ውስጥ በመግባቱ እስከ፲፱፻፴፩ ዓ/ም ድረስ አዚናራ ደሴት በእሥራት ቆይተው ተመልሰዋል። በእሥር ቤቱ ውስጥ በተካሄደው ምርመራ ብላታ አየለ ለኢጣልያ አስተዳደር ታማኝነታቸውን ያስመሰከሩና በወገኖቻቸው ላይ በተደረጉ እርምጃዎች የተባበሩ እንጂ በእሥራት መቀጣት እንደሌለባቸው የተረጋገጠ ሲሆን፤ በዚሁ ዓይነት የተመሰከረላቸውን ሌሎችንም ኢትዮጵያውያን መኳንንትን ጣሊያኖቹ በአስቸኳይ ወደአገራቸው እንዲመልሷቸው ያበረታታቸው ጉዳይ ደግሞ ሰኔ ፮ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ዘርዓይ ድረስ የተባለው የእሥረኞቹ አስተርጓሚ የነበረ ኤርትራዊ በብዙ የሮማ ዜጎች ላይ ያደረሰው ጉዳት ነው። ከድል በኋላ እስከ ታኅሣሥ ግርግር ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በድል አድራጊነት ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፻፴፫ ዓ/ም አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ፤ ብላታ አየለ ለጣሊያኖች በማደራቸውና ወገኖቻቸውን በመክዳት ስላደረሱባቸው ጉዳት በመቀጣት ፋንታ፣ ግንቦት ፫ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም የፍርድ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። ብላታ አየለ ገብሬ በሎንዶን የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት አምሥተኛው ዋና መላክተኛ ሆነው ከመስከረም ፯ ቀን ፲፱፻፴፭ ዓ/ም ጀምሮ የኤርትራው ተወላጅ ብላታ ኤፍሬም ተወልደ መድኅን እስከተኳቸው ጥቅምት ፳፱ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ድረስ አገልግለው ወደኢትዮጵያ ሲመለሱ በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት ምክትል ገዥነት፤ የጠቅላይ ግዛቱም ገዥ እንደራሴ ሆነው እስከ ፲፱፻፵፯ ዓ/ም ሠርተዋል። ከዚህ ሥራ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ያመሩት ወደ ፍርድ ሚኒስትርነት ሲሆን እስከ ፲፱፻፵፱ ዓ/ም ድረስ በቆዩበት ወቅት በነጋሪት ጋዜጣ ቁ ፩/፲፱፻፶፪ በተለይ የወጣውን “የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የፍትሐ ብሔር ሕግ” ቅንብር መርተዋል። ከፍርድ ሚኒስትርነት ክቡር ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው ሊቀ መንበርነት በሚመራው የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት በአባልነት ተዘዋውረው በዘውድ አማካሪነትም ሲሠሩ እስከ ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ቆዩ። የሕይወት ፍጻሜ በወንድማማቾቹ ጄነራል መንግሥቱ እና ገርማሜ ንዋይ የተጠነሰሰው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ማክሰኞ ታኅሣሥ ፬ ቀን ሲጀመር በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ከታሠሩት ለትላልቅ መሳፍንት፣ መኳንንቶችና ዋና ሚኒስቴሮች መኻል አንዱ ብላታ አየለ ገብሬ ነበሩ። ዓርብ ታኅሣሥ ፯ ቀን የሙከራው ኃይል እየተዳከመ በአንጻሩ ደግሞ ተቃዋሚዎቻቸው እያደር እየጎለመሱ መሄዳቸውን የተገነዘቡት ሽብርተኞች በቁጥጥራቸው ላይ የነበሩትን ሃያ መሳፍንት፣ መኳንንት፣ ሚኒስትሮችንና መኮንኖችን ወደ አረንጓዴ ሳሎን ካዛወሩ በኋላ ከተያዙት ሃያ ሰዎች ውስጥ ከተረሸኑት አሥራ-አምስት መኳንንትና ባለ-ሥልጣናት መኻል ብላታ አየለ ገብሬ አንዱ ነበሩ። ዋቢ ምንጭች ታዴዎስ ታንቱ (ዶክቶር)፤ “አውደ ታሪክ” ፍትህ ቅፅ ፭ ቁጥር ፻፹፬ (ሚያዝያ ፲፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም) ከበደ ተሰማ (ደጃዝማች)፤ “የታሪክ ማስታወሻ” ፤ (፲፱፻፷፪ ዓ/ም) ደምስ ወልደ ዐማኑኤል (ደጃዝማች) ፤ 'ሕገ መንግሥትና ምክር ቤት'፤ኹለተኛ መጽሐፍ ፥ አዲስ አበባ፥ ጥቅምት፡፲፱፻፶፩ ዓ/ም የኢትዮጵያ ካቢኔ አባላት
50605
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B5%E1%88%B5%E1%89%B5%20%E1%8A%A0%E1%88%AD%E1%88%B4%E1%88%9B
ቅድስት አርሴማ
ቅድስት አርሴማ ፣ ሂርፕሲም (አርሜኒያዊት) እንዲሁም ሪሂፕሲም ፣ ሪፕሲም ፣ አርብሲማ ወይም አርሴማ ተብላ የምትጠራ ሮማዊ መሰረት ያላት ሰማዕት ነበረች። እርሷ እና ባልደረቦችዋ የሰማዕትነት አክሊል የተቀዳጁ የመጀመሪያዎቹ የአርሜንያ ሰማዕታት እንደሆኑ ተደርገው ይታያሉ ። እናታችን ከአባቷ ከቅዱስ ቴዎድሮስና ከእናቷ ቅድስት አትናሲያ በስዕለት ተወለደች ። ቤተሰቦቿ እግዚአብሔርን በቅንነት ያገለግሉ ከነበሩ ከከበሩ ካህናት ወገን እንደነበሩ የገድሏ መጽሐፍ ይነግረናል ። ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ቅዱሳት መጻሕፍትን ከቤተሰቦቿ በሚገባ የተማረች፤ የተማረችውንም በተግባር የተረጎመች፤ በጸሎት ሕይወት የምትተጋ ከቅዱሳት አንስት አንዷ ናት ። ገድልዋ እደሚያስረዳው ድንግል እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው ። መድኃኒታችን ክርስቶስ በወንጌል እንዳለው "በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትምና ።" የሰማዕቷ ሕይወት በፊታችን እንደ ብርሃን ተገልጦ ይታያል ። ቅድስት አርሴማ እንደ ልጅ ወላጆቿን በመታዘዝ ደስ ያሰኘች ቡርክት ናት ። ቅድስት አርሴማ ይሕ ቀረሽ የማይሏት ውብ ናት ። ቅድስት አርሴማ ድንግል ናት ። ቅድስት አርሴማ ባሕታዊት ጻድቅ ናት ። ቅድስት አርሴማ ኃያል ሰማዕት ናት ። ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ፦ አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ቅዱስ ጐርጐርዮስ የታላቋ ሰማዕት ቅድስት አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው ። በዜና ሰማዕታት ተጽፎ እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች ነበሩበት ። ፩.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት ። ፪.ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት ። ፫.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት ። ቅዱሱ ሦስቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ መሆን ቻለ ። ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት ። መከራው በጣም ገፍቶ እስከ መጣበት ጊዜ ድረስ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ሆነው ይጸልዩ፣ ይጾሙ ፣ ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር ። ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስ ጻድቃን የምንላቸው ። በኋላ ግን ማኅደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ በመልኳ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ መቶ ሃያ ሰባት ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ ተሰደደ ። በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ፤ ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው ። የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ ለመውጣት ተገደደ ። በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግስት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ ። በሚያገኛት ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር። መከራው ግን አለቀቃቸውም ። ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከበት ። ድርጥዳስ ግን ለራሱ ፈለጋት ። የሰማዕትነትዋ መነሻ ይቺ ታላቅ ሰማዕት በነበረችበት ዘመን በአርመን የነገሠው አረማዊ ንጉሥ ይኸው ድርጣድስ ይባላል፡፡ ይህ ንጉሥ እግዚአብሔር አምላክ በሙሴ ላይ አድሮ "ቀልጠው የተሠሩትን የአማልክት ምስሎች ለአንተ አታድርግ" ብሎ የተናገረውን በመቃወም ለጣዖት የሚሰግድ ፀሐይንም ያመልክ ነበር ዘጸ.፴፬ ቁ.፲፯ ፡፡ በዘመኑ የነበሩ ክርስቲያኖችን "እኔ ለማመልከው "አምላክ" ወይም ጣዖት መስገድ አለባችሁ ፤ ይህን የማታደርጉ ከሆነ ትእዛዜን ጥሳችኋልና መከራ ይጸናባችኋል" የሚል ዐዋጅ በማውጣት ክርስቲያኖች ለስቃይ እዲጋፈጡ ሆ ፡፡ ጨካኙ ንጉሥ ድርጣድስ ይህን ትእዛዙን ባለማክበራቸው መከራና ስቃይ ያደረሰባቸው ክርስቲያኖች ቁጥራቸው ፻፳፯ ነበር ። የቅድስት አርሴማ ውሳኔ ቅድስት አርሴማም ይህን አይታ ከክርስቲያን ወገኖችዋ ጋር ወግና ስለክርስቶስ መመስከር ጀመረች ። የንጉሡም አገልጋይ በደም ግባቷና በንግግሯ ማማር ተደንቆ በዚች በፈቃዷ ሰማዕትነትን ልትቀበል በወደደች ሴት ምንም ሊያደርግባት ስላልወደደ ወደ ንጉሡ ወደ ድርጣድስ ከሃያ ሰባቱ ክርስቲያኖች ጋር ወሰዳት ፡፡ ንጉሡም ብዙ የተነገረላትን ወጣት ሲያይ በውበቷና በንግግሯ ተማርኮ ለዓለማዊ ደስታውና ፍላጎቱ ተመኛት ፡፡ ሚስት ትሆነው ዘንድ አብዝቶ ተማጸናት ፡፡ እጅ መንሻና ማታለየ የዚህን ዓለም ወርቅና ብር አቀረበላት ፡፡ ቅድስት አርሴማ ግን መልክ ረጋፊ ፤ የዚህ ዓለም ሀብትም ከንቱ እንደሆነ ስለምታውቅ በዓላማዋ ጸናች! ንጉሡንም "እኔ የንጉሥ ክርስቶስ ሙሽራ እንጂ የዚህን ዓለም አላፊ ጠፊ የሆነውን ገንዘብና ደስታ የምሻ አይደለሁም ፡፡" በማለት መለሰችለት ፡፡ የንጉሡም መልስና ዕድሉ ይህን በሰማ ጊዜ ሊያስፈራራትም ሞከረ ። ዓይኑዋ አያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው ። ኣልሳካልህ ቢለው በኣደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞከር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው ። እጅግ ስላፈረ ኣስገረፋት ኣሰቃያት ኣይኑዋንም አወጣ ። በመጨረሻም አንገቱዋን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት ። ከነገሩ ሁሉ በህዋላ ድርጣድስና ባለምዋሎቹ ለኣደን በሔዱበት እርኩስ መንፈስ ወደ ኣውሬነት ቀየራቸው ። የንጉሱ እንሰሳ (አውሬ) መሆን በአርሜኒያ ታላቅ ድንጋጤ ፈጠረ ። የንጉሡ እህት ስታለቅስ በራዕይ ተገልጾላት " ጎርጎሪዮስን ከተቀበረበት ካላወጣቹህ አትድኑም " ኣለቻቸው ። ወዲያውም ቆፍረው አወጡት ። ቅዱሱ እንደወጣ ዕረፍት አልፈለገም ፣ ለአስራ አምስት ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን የቅድስት አርሴማና የ ሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው ።ድርጣድስና ባለምዋሎቾንም ወደ በርሃ ሔዶ ፈወሳቸው ። የቅድስት አርሴማ አጽም በአስራ አራተኛው ክፍለ ዘመን ከሌሎች ሰማዕታት አጽም ጋር ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ አባቶቻችን በትውፊት ይናገራሉ ።
50210
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B0%E1%8D%8D%E1%8A%90%E1%8C%8D
ሰፍነግ
ሰፍነጎች በእንስሳት የዘር ግንድ ላይ እጅግ ጥንታዊውንና የታችኛውን ቦታ ይዘው ይገኛሉ። ልብም ሆነ አንጎል የሌላቸው መሆኑ አይገዳቸውም ሰፍነጎች ከዕፅዋት ወገን የሚመደቡ ቢመስሉም አርስቶትልና ትልቁ ፕሊኒ በትክክል ከእንስሳት ክፍል መድበዋቸዋል። ሊቃውንት በመላው ዓለም በሚገኙ ውቅያኖሶችና ሐይቆች ቢያንስ 15,000 የሚያክሉ የሰፍነግ ዝርያዎች ይገኛሉ ብለው ይገምታሉ። እነዚህ ሁሉ ሰፍነጎች በቅርጽም ሆነ በቀለም እጅግ የተለያዩ ናቸው። ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል ቀጭን ጣት፣ ጉርድ በርሜል፣ የተዘረጋ ምንጣፍ፣ የሚያምር ማራገቢያና የጠራ ብርሌ የመሰለ መልክ ያላቸው ሰፍነጎች አሉ። አንዳንዶች ከስንዴ ቅንጣት ያነሱ ሲሆኑ ሌሎች ደግሞ ከሰው የሚበልጥ ቁመት አላቸው። አንዳንድ ሰፍነጎች በመቶ የሚቆጠር ዕድሜ ሊኖራቸው እንደሚችል የሳይንስ ሊቃውንት ያምናሉ። ኢንሳይክሎፒዲያ ብሪታኒካ “ሰፍነጎች በቅርጻቸው፣ በአሠራራቸውም ሆነ በእድገታቸው ከሌሎች እንስሳት የተለዩ ናቸው” ይላል። ይህ ሊሆን የቻለው እንዴት ነው? ሰፍነጎች እንደ ሌሎቹ እንስሳት የውስጥ አካል የላቸውም። ታዲያ ልብ፣ አንጎልም ሆነ የነርቭ አውታር ሳይኖራቸው እንዴት በሕይወት መኖር ይችላሉ? በሰፍነግ አካል ውስጥ፣ ለመኖር አስፈላጊ የሆኑ ተግባራትን የሚያከናውኑ ጥቃቅን ህዋሳት ይገኛሉ። የተለየ ተግባር ያላቸው ህዋሳት ምግብ ያጠምዳሉ፣ ምግቦቹን ወደ ሰፍነጉ የተለያዩ የአካል ክፍሎች ያጓጉዛሉ ወይም ቆሻሻ ያስወግዳሉ። ሌሎች ህዋሳት ደግሞ የአጥንት ወይም የውጭ ሽፋን ክፍሎችን በትጋት ይሠራሉ። እንዲያውም አንዳንድ ህዋሳት አስፈላጊ ሆኖ በሚገኝበት ጊዜ ወደ ሌላ ዓይነት ህዋስ መቀየር ይችላሉ። ሰፍነጎች ከሌሎች እንስሳት ልዩ የሚያደርጓቸው ተጨማሪ ባሕርያት አሏቸው። በሕይወት ያለን ሰፍነግ በወንፊት ላይ እየደፈጠጥክ ብትበጣጥሰው ሴሎቹ ዳግመኛ ተሰብስበው የመጀመሪያውን ሰፍነግ ማስገኘት ይችላሉ። ሁለት ሰፍነጎችን አንድ ላይ አድርገህ ብትፈጫቸው ከጊዜ በኋላ ሴሎቹ ተለያይተው የቀድሞዎቹን ሰፍነጎች ይሠራሉ። ናሽናል ጂኦግራፊክ ኒውስ “በዚህ መንገድ ራሱን ከሞት ሊያስነሳ የሚችል አንድም ተክል ወይም እንስሳ የለም” በማለት ተናግሯል። በተጨማሪም ሰፍነጎች እንደ ሁኔታው በመለዋወጥ መራባት ይችላሉ። አንዳንድ ሰፍነጎች እንደ ሕዋ መንኮራኩር ተስፈንጥረው በመጓዝ በሌሎች አካባቢዎች ሊራቡ የሚችሉ ሴሎችን ይወነጭፋሉ። እነዚህ ሴሎች የሕይወት ተግባሮቻቸውን በሙሉ ለጊዜው አቁመው ረዥም ጉዞ ከተጓዙ በኋላ እንደገና ይነቁና “ከተጫኑበት” ወርደው አዲስ ሰፍነግ ያስገኛሉ። ሌሎች ሰፍነጎች እንደ አስፈላጊነቱ ወንዴና ሴቴ በመሆን በጾታዊ ተራክቦ አማካኝነት አዲስ ሰፍነግ ይወልዳሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ እንቁላል ይጥላሉ። የባሕር አጽጂዎች የሥነ እንስሳት ተመራማሪ የሆኑት አለን ኮሊንስ ሰፍነጎች “ከሌሎች እንስሳት የተለየ የአመጋገብ ሥርዓት አላቸው” በማለት ጽፈዋል። ሰፍነጎች በላይኛው ሽፋናቸው ላይ ከሚገኙ ጥቃቅን ቀዳዳዎች አንስቶ በመላው አካላቸው የተዘረጉ በርካታ ቱቦዎችና የተለያዩ ክፍሎች አሏቸው። በእነዚህ ቱቦዎችና ክፍሎች ግድግዳ ላይ ኮአኖሳይትስ የሚባሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ጥቃቅን ቀዛፊ ሴሎች አሉ። እያንዳንዱ ሴል ወደፊትና ወደኋላ እንዲቀዝፍ የሚያስችለው አለንጋ መሰል ጫፍ አለው። ቤን ሃርደር የተባሉ ጸሐፊ “[እነዚህ ሴሎች] ውኃ በሰፍነጉ ውስጥ ወደሚገኙ ሌሎች ሴሎች ያለማቋረጥ እንዲፈስ ሲያደርጉ ሌሎቹ ሴሎች ደግሞ በውኃው ውስጥ የሚገኙ የምግብ ቅንጣቶችን ይዘው እንዲዋሃድ ያደርጋሉ” በማለት ገልጸዋል። ሰፍነጎች የሰውነት መጠናቸውን አሥር እጥፍ የሚያህል ውኃ በየሰዓቱ በውስጣቸው እንዲያልፍ በማድረግ በውኃው ውስጥ የሚገኙ ምግቦችን፣ መርዛማ ኬሚካሎችንና እስከ 90 በመቶ የሚደርሱ ባክቴሪያዎችን ውጠው ያስቀራሉ። እንዲያውም የውኃው አፈሳሰስ በሚቀያየርበት ወይም በውስጣቸው የተጠራቀመውን ደለል ማስወገድ በሚፈልጉበት ጊዜ የውኃውን መጠን የመቆጣጠር አሊያም የፍሰቱን አቅጣጫ የመቀየር ችሎታ አላቸው። ዶክተር ጆን ሁፐር “የሰፍነጎችን ያህል . . . ጥሩ የባሕር አጽጂዎች አይገኙም” ብለዋል። በሰፍነጎች ውስጥ የማያቋርጥ የምግብና የውኃ ፍሰት መኖሩ እንደ ሽሪምፕና ክራብ ላሉት ትናንሽ ፍጥረታት አመቺ መኖሪያ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። በአንድ ሰፍነግ ውስጥ 17,128 የሚያክሉ ነዋሪዎች ተገኝተዋል። በርካታ ባክቴሪያዎች፣ አልጌዎችና ፈንገሶች ከሰፍነጎች ጋር ተረዳድተውና ተደጋግፈው ይኖራሉ። አንድ ሰፍነግ በእርጥብነቱ ከሚኖረው ክብደት ውስጥ እስከ 50 በመቶ የሚሆነውን የሚይዙት ባክቴሪያዎች ናቸው። ሳይንቲስቶች፣ ሰፍነጎችና ተባባሪ ጥገኞቻቸው የአዳዲስ መድኃኒቶች ምንጭ ሆነው ሊያገለግሉ እንደሚችሉ ተስፋ ያደርጋሉ። እነዚህ መድኃኒቶች ኤድስን፣ ካንሰርን፣ ወባንና ሌሎች በሽታዎችን ለማጥፋት ጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚችሉ ያምናሉ። ሸርሊ ፖምፖኒ የተባሉ ተመራማሪ ይህን በሚመለከት “ተፈጥሮ፣ ኮምፒውተሮቻችን እንኳን ሊያቀናጁ ከሚችሏቸው የበለጡ ውስብስብና ጠቃሚ ሞለኪውሎችን ያመነጫል” ብለዋል። መስተዋት ዓይነት ነገር የሚፈጥሩበት ሁኔታ ብዙ ሰፍነጎች ለገላ መታሻ እንደምንጠቀምባቸው ሰፍነጎች ለስላሳ ሳይሆኑ ሻካራ ወይም ጠንካራ ናቸው። እነዚህ ሰፍነጎች ስፔኪዩልስ የሚባሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ጥቃቅን የመስታወት ቅንጣቶች አሏቸው። ስፔኪዩሎች በአጉሊ መነጽር ሲታዩ ያላቸው ውበትና ዓይነታቸው የተለያየ መሆኑ በጣም የሚያስገርም ነው። እነዚህ ስፔኪዩሎች በተለያየ መንገድ እንደ ሰንሰለት ሲያያዙ በጣም ውስብስብ የሆነ አጽም፣ የመከላከያ መሣሪያ እንዲያውም ቁመቱ እስከ 3 ሜትር ውፍረቱ ደግሞ እስከ 1 ሴንቲ ሜትር የሚደርስ ገመድ ይፈጥራሉ። አንድ ሥጋ በል ሰፍነግ ፍጥረታትን አድኖ የሚይዝበት ባለ መንጠቆ መረብ አለው። ጥልቅ በሆነ ባሕር ውስጥ የሚገኘውና የቬነስ አበባ ቅርጫት እየተባለ የሚጠራው የሰፍነግ ዝርያ ስፔኪዩሎችን ተጠቅሞ በጣም ውብ የሆነ የአበባ ጥልፍ መሥራት ይችላል። እነዚህ እንደ ብርሌ የጠሩ የመስታወት ቃጫዎች ለስልክ ማስተላለፊያ የሚያገለግሉትን ዘመናዊ ፋይበር ኦፕቲክ ገመዶች ይመስላሉ። አንድ ሳይንቲስት “እነዚህ ሕያው ቃጫዎች በጣም ጠንካራ ናቸው” ብለዋል። አክለውም “በኃይል ብትቋጥራቸው እንኳ እንደ ሰው ሠራሾቹ ቃጫዎች አይበጠሱም” በማለት ተናግረዋል። እነዚህ ውስብስብ ቃጫዎች በባሕር ውስጥ እንዲሁም ዝቅተኛ የሙቀት መጠን ባለበት አካባቢ እንዴት ሊፈጠሩ እንደሚችሉ ሳይንቲስቶች በውል ሊረዱት አልቻሉም። የቤል ቤተ ሙከራ ባልደረባ የሆኑት ቼሪ ሙሬይ “በዚህ መንገድ፣ ውስብስብነት የሌለው ይህ ፍጥረት ፋይበር ኦፕቲክ ገመዶችንና እንደ ሴራሚክ ያሉ ነገሮችን በመሥራት ረገድ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት አገልግሏል” ብለዋል።
50385
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%89%A3%E1%88%B5%E1%88%8A%E1%8B%AE%E1%88%B5%20%E1%8B%98%E1%89%84%E1%88%A3%E1%88%AD%E1%8B%AB
ቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ
ባስሊዮስ ዘቄሣርያ በሌላ አጠራሩ ታላቁ ቅዱስ ባስሊዮስ (በግሪክ: ) (በእንግሊዘኛ ሲነበብ ባዚል ኦፍ ሢዛሪያ)በቀጰዶቂያ የቄሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ነበር ። የንቂያን የሊቃውንት ጉባዔ የሚደግፍና አርያኒዝምንና የአፖሊናረስን ተከታዮችን የክርስትና አመለካከት ተቃውሞ ትክክለኛውን መንገድ ያስተማረ ታላቅ አሳማኝ የሃይማኖት ፈላስፋና መሪ ነበር ። ቅዱስ ባስሊዮስ ከሃይማኖት ፈላስፋነቱ ሌላ ድሆችንና ኑሮን ማሸነፍ ያቃታቸውን በመንከባከብ ይታወቃል ። በተጨማሪም የማኅበራዊ ኑሮ ፣ የሥርዐተ ጸሎትና የጉልበት ሥራ ለገዳማዊ ኑሮ መመሪያን መሥርቷል ። ባስሊዮስ ከቅዱስ ጳኩሚስ ጋር የማኅበራዊ ገዳማዊነት አባት ተብሎ በምሥራቃዊ ክርስትና ይታሰባል ። ዳሮግን በምሥራቅም በምዕራብም በቅዱስ ደረጃ ነው የሚከበረው ። እነዚህ ሁለት ጎራዎች ታላቅ የቤተክርስቲያን አባት የሚለውን ስያሜ ከዮሐንስ አፍወርቅና ከግሬጎሪዮ ናዚያንዘስ ጋር ሰተውታል ። የቀደመ የሕይወት ታሪኩና ትምህርቱ ባስሊዮስ ከቀዳማዊ ባስሊዮስና ከኤሚልያ የቄሣሪያዋ በ፫፻፳ ዓም አካባቢ በቀጰዶቂያ ተወለደ ። እናትና አባቱ እግዚአአብሔርን በጣም የሚወዱና ጸሎተኞች የነበሩ ሰዎች ነበሩ ። የእናቱ አባት ከቆስጠጢኖስ ፩ኛ በክርስትና ማመን በፊት ሰማዕት ሆኖ ያለፈ ሰው ነበረ ። ጸሎተኛ ባልቴቱ ማክሪናም የጎርጎርዮስ ታውማታርገስ (የኒዎ ቄሣርያን ቤተክርስቲያን በአቅራቢያው የመሠረተ) ተከታይ የነበረች ባስሊዎስንና አራቱን ወንድሞቹንና እህቱን ፣ ወጣትዋ ማክሪና ፣ ናውክራቲየስ ፣ ጴጥሮስ የሰባስቴውንና ፣ ጎርጎርዮስ የኒሳውን (ወደፊት ታላቅና የተከበሩ ቅዱሳን የሚሆኑ) በክርስትና ሃይማኖት ሥርዐት አሳደገች ። ባስሊዮስ በቄሣርያ ማዛካ ቀጰዶቂያ በአሁኑ ዘመን አጠራር ካይዜሪ (ቱርክ) ትምህርት ቤት በ፫፻፵፪ ፵፫ ዓ.ም.አካባቢ ተምሩዋል ። እዛም ጎርጎርዮስ ናዚያንዘስን የረጅም ጊዜ ጉዋደኛ የሚሆነውን ተዋውቋል ። ባስሊዮስና ጎርጎርዮስ አንድላይ በመሆን ለከፍተኛ ትምህርትና በተጨማሪ የሊባኒየስን ትምህርታዊ ንግግር ለማጥናት ወደ ቁስጥጥኒያ አምርተዋል ። ሁለቱ በአቴንስ በ፫፵፪ ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል ። በዛም ቆይታቸው ጁሊያን ዘአፖስቴት ወደፊት ንጉሥ የሚሆን ተማሪ ተዋውቀዋል ። ባስሊዮስ አቴንስን በ፫፵፰ ለቆ ወደ ግብፅና ሶርያ ከተጉዋዘ በኋላ አገሩ ቄሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር ቆየ ። የባስሊዮስ ሕይወት ኢውስታቲየስ የሴባስትን ኃይለኛ የማሳማን ችሎታና ጥሩ ግብረገብ ያለውየተዋወቀ ጊዜ ሕይወቱ ሙሉበሙ ተቀይሩዋል ። ከዚህም የተነሳ ሕጋዊ የማስተማር ሥራውን ትቶ ሕይወቱን ለእግዚአብሔር ሰጠ ። ይህንንም የመንፈሳዊ ሕይወቱን መነቃቃት የሚያሳይ ጽሑፍ እንደሚከተለው አስቀምጦታል ፡ ብዙውን ጊዜዬን በማይረቡ ነገሮች አሳለፍኩ የወጣትነት ዕድሜዬንም በከንቱ ልፋትና እግዚአብሔር ሞኝነት ላደረገው ጥበብ ። በቅጽበት ከኃይለኛ እንቅልፍ ነቃሁ የወንጌልንም እውነተኛ ብርሃን አጥብቄ ያዝኩ የዚህንም ዓለም ንጉሦች ጥበብ ባዶነት ተረዳሁ ። ባስሊዮስ በአኔዚ ከተጠመቀ በኋላ ባስሊዮስ በ፫፻፵፱ ዓ ም ወደ ፍልስጤም ፣ ግብፅ ፣ ሶርያ እንዲሁም መስጴጦምያ የመመንኮስንና የገዳማዊነት ትምህርት ለማጥናት ሄደ ። ያለውን ሐብት በሙሉ ለድሆች አድሎ እንደጨረሰ ወደ ምነና በፖንተስ ኒዎሢዛርያ (በዘመኑ አጠራር ኒክሳር ቱርክ) ቤተክርስቲያን ገባ ። ባስልዮስ ይህን የገዳማዊ ኑሮ ቢያከብረውም ለሱ እንዳልተጠራ ተረዳ ። የሴባስቴው እዩስታቴየስ እጅግ የታወቀ መኖክሴ በፖንተስ አካባቢ ባስሊዮስን ያስተምረው ነበር ። በዶግማ ላይ ግን ይለያዩ ነበር ። ይልቁን ባስሊዮስ በመንፈሳዊ ማኅበራዊ ኑሮ ተሳበና በ፫፻፶ በአስተሳሰብ ከእሱ ጋር የሚመሳሰሉትን የክርስትና ደቀመዝሙሮች ወንድሙን ጴጥሮስን ጨምሮ ማሰባሰብ ጀመረ ። አንድላይ ሆነው በቤተሰቡ ርስት ላይ አኔዚ አጠገብ ገዳም መሠረቱ ። በጣም ግልፅ ለማረግ (በዘመኑ አጠራር ሶኑዛ ወይም ኡሉኮይ የዬሲሊርማክ ባሕርና የኬልኪት ባሕር የሚገናኙበት ቦታ ላይ ማለት ነው ።). ባልተቤትዋ እናቱ ኤሚልያ ፣ እህቱ ማክሪናና ሌሎች ሴቶችም ራሳቸውን ለቅዱስ ተግባር መጽዋት በማድረግ ከባስሊዮስ ጋር ተባበሩ ። (ይህን ማኅበረሰብ የመሠረተችው እህቱ ማክሪና ናት የሚሉም አሉ) ። ቅዱስ ባስሊዮስ እዚህ ባታ ላይ ስለ ገዳማዊ ማኅበራዊ ኑሮ ጽፎ ነበር ። ጽሁፉ ግን ለምሥራቃዊ ክርስትና ዕድገት ከፍተኛ ምክኒያት ሆንዋል. በ፫፻፶ዓ ም ባስሊዮስ ጉዋደኛውን ጎርጎሪ (ግሬጎሪ) የናዚያነስን በአኔዚ እዲቀላቀል ጋበዘው። ጎርጎሪዮም (ግሬጎሪ) እንደመጣ በኦሪጄን ፊሎካሊያ የኦሪጄን ሥራዎች ስብስብ ላይ ጥናት ማድረግ ጀመሩ ። ከዚህም በኋላ ግሬጎሪ ወደ ናዚያነስ ወደ ቤተሰቦቹ ለመመለስ ወሰነ ። ባስሊዮስ የቁንስጥጢናውን የሊቃውንት ጉባዔን ፫፻፶፪ ዓ ም ተሳተፈ ። በመጀመሪ ከኤዩስታቲየስና ከሆሞወሲያንስ ወገነ ፣ ግማሽ አራዊያን የሆነ የመናፍቅ ቡድን ፣ ወልድ ከአብ ጋር ተመሳሳይ እንጂ አንድ ባሕርዪ ወይም አካል አይደለም ብለው ከሚያስተምሩ ጋር ማለት ነው። ሆሞወሲየንስ የአውኖሚየስን አርያኒዝም ይቃወማሉ ግን ደግሞ ከኒቂያ ጉባዔ ተከታዮች ጋር የሥላሴን አንድነት "ሆሞወሲዮስ" ከሚያስተምሩት ጋር መተባበር አይፈቅዱም ። በዚህም ቢሆን በዚያ የባስሊዮስ ጳጳስ ዲያኒየስ የቄሣሪያው የሚከተሉት የቀድሞውን ንቂያ ስምምነት ነበረ ። ባስሊዮስም ወዲያውኑ ሆሞወሲያንስን ጥሎ እንዲየውም ጠንካራ የኒቂያ ጉባዔ ውሳኔን ተከታይ ሆነ ። ባስሊዮስ በቄሣሪያ በ፫፻፶፬ ዓ ም ጳጳሱ ሜለቲየስ የአንጾኪያው ባስሊዮስን ዲያቆን አድርጎ ሾመው ። አውሰቢየስ ደሞ በቄሣሪያ ቤተክርስቲያን በ፫፶፯ ዓ ም ፕሬስቢተር እንዲሆን ሾመው ። እኒህ የቤተክህነት ጥያቄዎች የባስሊዮስን ምርጫ የማይመጣጠኑ ስለሆኑ የሥራውን አቅጣጫ እንዲቀየር አድርገዋል ። ባስሊዮስና ግሬጎሪ ናዚያነስ ለጥቂት ዓመት የአርያኒዝም መናፍቅ ትምህርት የቀጰዶቂያን ክርስቲያኖች ይከፋፍላል ተብሎ ስለሚያሰጋ ሲታገሉ ቆዩ ። በኋላም የማሳመኛ ንግግር በትልቅ ደረጃ ውድድር (ክርክር) ከታዋቂ አርያውያን ቴዎሎጂየንና ተናጋሪዎች ጋር ለማድረግ ስምምነት አደረጉ ።በንጉሥ ቫሌንስ ተወካዮች መሪነት ከተደረገው ክርክር በኋላም ግሬጎሪና ባስሊዮስ አሸናፊዎች ሆነው ወጡ ። ይህ መሳካት ለግሬጎሪና ለባስሊዮስ የወደፊት ሥራቸው በቤተክርስቲያን አስተዳዳሪነት መሆኑን አረጋገጠላቸው ። ቀጥሎም ባስሊዮስ የቄሣሪያን ከተማ አስተዳደር ወሰደ ። አውሰቢየስ ግን በባስሊዮስ ፈጣን እድገትና በማኅበረሰቡ ባገኘው ተቀባይነት በመቅናት ወደ ነበረበት የገዳም ብቸኝነት ኑሮ እንዲመለስ ፈቀደለት ። ቆይቶ ግሬጎሪ በዚም በዚያም ብሎ ባስሊዮስን እንዲመለስ አሳመነው ። ባስሊዮስም እንዳለው አደረገ በዚያችም ከተማ ለበርካታ ዓመት ውጤታማ አስተዳዳሪ ሆነ የተደነቀበትን ሥራ ሁሉ ለአውሰቢየስ ተወለት ። በ፫፻፷፪ ዓ ም አውስቢየስም ሞተ ባስሊዮስም እንዲተካው ተመረጠ በዛውም ዓመት የቄሣሪያ ጳጳስ ሆነ ። አዲሱ የቄሣርያ ጳጳስ ሹመቱ በተጨማሪ የፖንተስ ኤክስአርክና የሜትሮፖሊታን ጳጳስ (አምስት ጳጳሳትን የሚያካትት) ሲያስሰጠው ከአምስቱ አብዛኞቹ የአውስቢየስን ቦታ እንዲይዝ የማይፈልጉ ነበሩ ። ይህን ጊዜ ነው የሹመቱን ኃይል ለመጠቀም ያስፈለገው ። ባስሊዮስ ለሃይማኖቱ የጋለ ስሜት ያለው ፣ ትዛዝ ሰጪ ደግና ለሰው አዛኝ ነበረ ። በዛም ወቅት ድርቅ ባስከተለው ረሐብ ምክኒያት በግሉ ምግብና መጠጥ በማዘጋጀት ለድሆች አድልዋል ፣ ያገኘውን የቤተሰብ ውርሱንም እንደዚሁ ድሆች እንዲጠቀሙ በነበረበት ቤተክርስቲያን አካባቢ አድልዋል ። ባስሊዮስ ከብዙ የሃይማኖት መሪዎችና ቅዱሳን ጋር ደብዳቤ ተጻጽፍዋል ። ከ ደብዳቤዎቹም መካከል ያለማቋረጥ ሌቦችንና ሴቲኛአዳሪዎችን ለማዳን እንደሠራ የሚያሳዩ ይገኙበታል ። ከሱም ጋር የሚሠሩትን የቤተክህነት አገልጋዮች በሀብት ፍለጋ እንዳይፈተኑ በቀላል የካህን ኑሮ እንዲወሰኑና ብቁ የሆኑ የቤተክህነት ሠራተኞች ለቅዱስ ሥራ እራሱ ይመርጥ እንደነበር ያሳዩ ነበር ። ባለሥልጣኖችንም ፍትሕ ባጉዋደሉ ጊዜ ወይም ግዴታቸውን ባልተወጡ ጊዜ ከመተቸት ወደኋላ አይልም ነበር ። ይህን ሁሉ እያካሄደ በራሱ ቤተክርስቲያን ውስጥ ለሰፊ ማኅበረሰብ ምዕመናን ጠዋትና ማታ ያስተምርና ይሰብክ ነበር ። ከዚህ በላይ ከተባሉት በተጨማሪ ለብዙ ዓይነት መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሆን በቄሣሪያ ባዚሊያድ () የሚባል ሕንፃ ገንብቱዋል ። የሚያካትተውም ለምስኪኖች መኖሪያ ቤት ፣ ወደ መጨረሻ ዕድሜያቸው የደረሱ ሰዎች እንክብካቤ የሚደረግላቸው ቤትና የነዳያን ሐኪም ቤት ናቸው ። ግሬጎሪ ናዚያንዘስ አስተያየት ሲሰጥ የዓለም አስደናቂ ሥራዎች ብሎታል ። ስለ ሃይማኖቱ ስለ እውነት ያለው ኃይለኛ አቋም በተቀናቃኙ ውስጥ ያለውን ጥሩ ነገር እንዳይታየው አልጋረደውም ፣ ስለሰላምና መታደግ ሲል መስማማት ያለእውነት መስዋትነት የሚገኝ ከሆነ የእውነት መለኪያውን ደስ እያለው አይጠቀምበትም ነበር ። በአንድ ወቅት ንጉሡ ቫሌንስ የአርያን ፍልስፍና ተከታይ የነበረ የመንግሥቱን ተወካይ ሞደስተስን ቢቻል በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ከቀሪዎቹ የአርያን ቡድኖች ጋር እንዲስማሙ መልክተኛ አርጎ ወደ ባስሊዮስ ላከው ። የባስሊዮስ ግትር እምቢተኛነት ሞደስተስን "በዚህ ሁኔታ ማንም አናግሮኝ አያውቅም" ብሎ እዲናገር አረገው ። ባስሊዮስም ሲመልስ "ከጳጳስ ጋር ተደራድረህ አታውቅ ይሆናል" ብሎ መለሰለት ። ሞደስተስም ለአለቃው ለንጉሡ "ባስሊዮስ ኃይል እንጂ ሌላ ምንም አይመልሰውም" ብሎ ልኮለታል ። በወቅቱ ቫሌንስ ጦርነት እንደማይፈልግ ማንም ያውቅ ነበር ። ታዲያ በተደጋጋሚ ያልተሳካ ባስሊዮስን ከሥራው የማፈናቀል ሙከራዎች አደረገ ። ከዛም ራሱ ቫሌንስ ወደ ባስሊዮስ ቅዱሱን የጥምቀት በዓል በሚያከብርበት ዕለት መጣ ። በዛም ወቅት በባስሊዮስ በጣም ስለተደነቀ ለባዚሊያዱ ሕንፃ መሥሪያ መሬት ሰጠው ። ይህም መንግሥት በቤተክርስቲያን ላይ ያለውን ኃይል ወሰነው። ይህም ደግሞ እያደገ በመስፋፋት ላይ ያለውን አርያኒዝምን እንዲጋፈጥ አስገደደው ። ይህ አርያኒዝም ክርስቶስን በተወሰኑ መልክ ከአባቱ ጋር አንድ መሆኑን የሚያስክድ ፍልስፍና እየሰፋ በብዙ አካባቢ ተቀባይነት ሲያገኝ በተለይ በአሌክሳንድሪያ ብዙዎች ስለሚያውቁት ለቤተክርስቲያን አንድነት በጣም አስጊ ምክኒያት ሆኖ ተገኘ ። ባስሊዮስ በአትናቲዮስ እርዳታና ከምዕራብ ቤተክርስቲያን ግንኙነት በማድረግ ይህን የሆሞውሲያነስ ስሕተተኛነትና ያለመቀበል ያለውን ስሜት እውነት ለማረግ ብዙ ሞክሩዋል ። ችግሩ የመንፈስ ቅዱስን ማንነት ጥያቄ በመጣበት ጊዜ ተባብስዋል ። ባስሊዮስ ግን የመንፈስ ቅዱስን ከእግዚአብሔር አብና ከእግዚአብሔር ወልድ ጋር እኩል መሆኑን በማስረጃ አጥብቆ ያስተምርና ይሰብክ ነበር ሆሞዋሲዮስንም ከሱ አስተምሮ ጋር አያስተካክላቸውም ነበር ። ለዚህ በመጀመሪያዎቹ ፫፻፷፫ ዓም በኦርቶዶክስ አክራሪ አባቶች ይነቀፍ ነበረ ። አትናሲዮስ ግን ይደግፈው ነበር ። ከዶግማቲክ ልዩነት በስተቀረም ከሴባስቴው እዩስታቲየስ ጋር ያለውን ጉዋደኝነት ጠብቋል ። ባስሊዮስ ከጳጳሱ ዳማሰስ ጋር የጽሁፍ ልውውጥ በማድረግ ጳጳሱ መናፍቃን በምሥራቅም በምዕራብም እንዲወገዙ ተስፋ አድርጎ ነበር ነገር ግን የጳጳሱ ወላዋይ አቋም የባስሊዮስን ቆራጥነት አሳዝኖት ተስፋውን አድብዝዞበታል ። ከሥራዎቹ በጥቂቱ አባቶቻችን እንዳስተማሩን ቅዱሱ ሊቅ ከሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ሊቃውንት አንዱ ነው ። ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊንም ያስተማረው እርሱ ነው ። ነገር ግን ቅርብ ጊዜ ከድረ ገጾች ታሪክ እየገለበጡ የሚጽፉ አንዳንድ ወንድሞች ይህንን የሚያፋልስ ነገር ጽፈው ተመልክተናል ። ቅዱስ ባስልዮስ ገዳማዊ ጻድቅ፣ ባለ ብዙ ምሥጢር ሊቅ ፣ የብዙ ምዕመናን አባት፣ የቂሣርያ ሊቀ ጳጳሳት፣ ባለ ብዙ ተአምራትና ከከዊነ እሳት (ከፍጹምነት) የደረሰ አባት ነው ። ለመጀመሪያ ጊዜ የነዳያንን ሆስፒታል በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ያስገነባ እርሱ ነው። እጅግ ብዙ ድርሰቶች አሉት ። መጽሐፈ ቅዳሴውንም ዛሬ በምናውቀው መንገድ ያሰናሰለው እርሱ ነው። ለምዕመናን የሚጠቅሙ ብዙ ሥርዓቶችን ሠርቶ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን ተርጉሟል ፣ በየዕለቱም የሚጸለዩትን "ውዳሴ አምላክ" "የኪዳን ጸሎት" "ሊጦን" የተባሉትን መጸሐፍት የሚያካትት መጽሐፈ ጸሎትን ያዘጋጀ እሱ ነው ። እሱ በጻፋቸው መጸሐፍት ላይ ተመርኩዘው ብዙ አባቶች ጽፈዋል ። በመጽሐፈ ስንክሳር ጥር ፮ ቀን በሚነበበው የቅዱሳን ገድል ላይም የሠራው ታላቅ ተአምር ተጽፎ ይገኛል ። ታዲያ ይህ ሊቅ ቅዱስና ጻድቅ ሰው ብዙ ድንቆችን ሠርቷል ። ባሰሊዮሰ የፊት ገጽታ መዛባቱ ከመጠናቀቁ በፊት ሞተ።በጉበት በሽታ ተሠቃይቷል።ከልክ ያለፈ እርባናዊ ድርጊቶችም ለቀድሞ ሕይወቱ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።የታሪክ ምሁራን ባሰሊዮሰል በትክክል ስለሞተበት ቀን አይስማሙም።የቂሳርያ፣የፓቶኮፕተሪዮስ ወይም “ባዚሊያድ”፣እንደ ድሃ ቤት፣ ሆስፒታል እና ሆስፒታሎች ፊት ለፊት የነበረው ታላቁ ተቋም ለድሆች የባሰሊዮሰ ተከታታይ የምጽዓት መታሰቢያ ሆነ።ብዙዎቹ የቅዱስ ባሰሊዮሰል ጽሑፎች እና ስብከቶች በተለይም በገንዘብ እና በንብረት ላይ በተነሱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ያሉትን ክርስቲያኖችን መፍታተናቸውን ቀጥለዋል። ሰነ ጽሑፍ የባስሊዮስ ዋና ሥነ-መለኮታዊ ጽሑፎች ስለ መንፈስ ቅዱስ ሲሆን በቀደመ የክርስትና ባህል (የመንፈስ ቅዱስን መለኮትነት ለማረጋገጥ) እና የእግዚአብሔር ፍራቻ ለሌለው ለኤውኖሚየስ የነቀፋ መጻሕፍት በ፫፻፶፮ ዓ.ም. ፣ የአኒሞኒያን የአሪያኒዝም ዋና ተዋናይ የሳይዛይከሱ ኤውኖሚየስን የሚቃወም ሦስት መጻሕፍት ። የመጀመሪያዎቹ ሦስት የማመሳከሪያ መጻሕፍት የእርሱ ሥራ ናቸው ፡፡ የአራተኛውና አምስተኛው መፅሃፍ ደራሲው ግን እንደ ተጠራጠረ ያስመስለዋል ። ባስሊዮስ ዝነኛ ሰባኪ ነበር ፣ ባብዛኛዎቹ ሰበካዎቹና የጾም ጊዜ ትምህርቶቹ በሄክሰሮንሮን (ማለት ፡ ሄክሳምሮስ ፣ “የፍጥረት ስድስት ቀናት”) ፣ በላቲን: (ሄክሳሮን) ላይ ያተኩሩ ነበር በተጨማሪም ለጸሎት የተጻፉ የዳዊት መዝሙሮች ከላይ እንደጠቀስናቸው ውዳሴ አምላክን የመሳሰሉ ጨምሮ በርካታ መጻሕፍት ይቀርባሉ ፡፡ አንዳንዶቹ በ፫፻፷ዎቹ ረሃብ ላይ ለሥነ ምግባር ታሪክ ዋጋ የሚሰጡ ናቸው ፣ ሌሎች ለሰማዕታት እና ለጽሑፍ ቅርሶች የተከፈለውን ክብር ያሳያሉ ። የጥንታዊ ሥነ ጽሑፍ ጥናት ላይ ለወጣቶች የተላለፈው መልዕክት የሚያሳስበው ባስሊዮስ በመጨረሻ የራሱ አስተምህሮ በራሱ ላይ ተጽዕኖ እንዳሳደረበት ያሳያል ፣ ይህም የጥንታዊ ሥነ-ጽሑፋዊ ጠቀሜታ አድናቆት እንዲያድርበት አድርጎታል። በትርጓሜው ውስጥ ባሰሊዮሰ ለኦሪጀን እና ለቅዱሳት መጻሕፍት መንፈሳዊ ትርጓሜ አስፈላጊነት ከፍተኛ አድናቆት ነበረው ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ሥራው ላይ “ቀጥተኛውን ቃል ወስዶ እዚያ ለማቆም ፣ በአይሁዲዝም ሥነ-ጽሑፍ መሸፈኛ ልብ መሸፈን ነው” የሚል ማረጋገጫ ሰጥቷል ፡፡ መብራቶች ፀሐይ በምትበራበት ጊዜ ከንቱዎች ናቸው ፡፡ እርሱ በመሠረተ ትምህርት እና በቅዱስ ቁርባን ጉዳዮች ውስጥ የመጠባበቂያ አስፈላጊነት ደጋግሞ አበክሮ ገልጽዋል ፡፡ በተመሳሳይ ጊዜ የአንዳንድ ዘመናትን የዱር ቅኝቶች ይቃወም ነበር። ይህን በተመለከተ ፣ እንዲህ ሲል ጽፍዋል : እኔ በሌላው ሥራ በበለጠ በእኔ ሥራ ያነሰ በሚሆን የተዘበራረቀ የምሳሌ ህጎችን አውቃለሁ ፣ በርግጥም አሉ የቅዱሳት መጻሕፍትን የጋራ ስሜት የማይቀበሉ ፣ ውሃን ውሃ አይደለም የሚሉ ፣ በአንድ ተክል ውስጥ ወይም ዓሳ ውስጥ የራሳቸውን የደስታ ምኞቶች የሚያዩ ፣ የእንስሳዎችን እና የዱር አራዊትን ተፈጥሮ ለምሳሌዎቻቸው እንዲስማሙ አድርገው ለውጠው ከግምትዎቻቸው ጋር እያስማሙ ምሳሌዎች የሚጽፉ ፣ እንደ ሕልም አስተርጓሚዎች ሕልሞችን የራሳቸውን መጨረሻ እንዲያገለግሉ የሚያደርጉ ። የእሱ የመራባት ዝንባሌ በሞራሊያ እና በደኢታካ (አንዳንዴም የቅዱስ ባሰሊዮሰ ህጎች በተተረጎመው) እና በሥርዓት በዓለም ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉ የሥነ-ምግባር መመሪያዎች ይታያሉ ፡፡ የታላቁ አስኬቲከን እና አናሳ አስኬቲከን የተባሉትን የሁለቱ ሥራዎች ትክክለኛነት በተመለከተ ጥሩ ውይይት ተደርጓል ፡፡ የእሱ ሥነ-መለኮታዊ ተግባራዊ ገጽታዎች የተገለፀው በሥነ-ጽሑፍ ጽሑፎች እና በሞራል ስብከቶች ውስጥ ነው ፡፡ ስለዚህ ፣ ለምሳሌ ፣ የጎረቤቶቻችንን ተፈጥሯዊ ፍላጎቶች (ለምሳሌ ፣ ረሀብ ፣ ጥማትን) እንደራሳችን አድርገን እንድንመለከት የሚረዳን የጋራ ተፈጥሮአዊ ተፈጥሮአችን እንደሆነ ያስረዳናል ። ምንም እንኳን ሌላ ግለሰብ ቢሆን ። ሦስት መቶ ደብዳቤዎች ፣ በሽታ እና ቤተክርስቲያናዊ አለመረጋጋት ችግሮች ቢኖሩም ተስፋ ሰጭ ፣ ርህራሄም እና ተጫዋች የነበረ ፣ ሀብታም እና ታዛቢ ተፈጥሮውን ያሳያሉ። እንደ አንድ የማሻሻል እርምጃ ዋና ተግባሩ የሕግ ሥነ-ሥርዓቱን ማደስ እና የምስራቅ ገዳማትን ተቋማት ለውጥ ለማምጣት ነበር ፡፡ አብዛኛዎቹ የእሱ ሥራዎች እና ለእሱ በጥቂቶች የተጻፉ ናቸው የተባሉት የተለያዩ ጥራት ያላቸው የላቲን ትርጉሞችን በሚያካትተው ፓትሎሎጂ ግሪካ ውስጥ ይገኛሉ። በርከት ያሉ የቅዱስ ባሰሊዮሰ ሥራዎች በሃያኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በእነ ሶርስ ክሪኔኔስ ክምችት ውስጥ ይታያሉ ፡፡ ሥነ-ምግባራዊ አስተዋፅዎች በስደት ዘመን ማብቂያ ላይ እንደመጣ ፣ የቂሳርያ ባስሊዮስል በክርስቲያናዊ ሥነ-ስርዓት ታሪክ ውስጥ በጣም አስፈላጊ ቦታን ይይዛል ፡፡ የባስሊዮስል ሥነ ምግባራዊ ተጽዕኖ በቀደሙት ምንጮች ውስጥ በሚገባ ተረጋግጥዋል ፡፡ ምንም እንኳን በአሁኑ ጊዜ ስሙን የሚሸከሙት መለኮታዊ ሥነ- ሥርዓት የትኞቹ ክፍሎች በትክክል እንደሆኑ ማወቅ ከባድ ቢሆንም በብዙዎች የምሥራቅ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የተመዘገቡት የጸሎት አካላት እጅግ ፀንተዋል ፡፡ የባሲል ስም የሚሸከሙት አብዛኞቹ [ሥነ ስርዓት | ሥነ-ሥርዓቶች] አሁን ባሁኑ መልኩ ሙሉ ሥራቸው አይደሉም ፣ ሆኖም ግን በዚህ መስክ ውስጥ የ ባስሊዮስል ሥነ ሥርዓቶችን በማዘጋጀት እና በቤተክርስቲያን ውስጥ ዝማሬዎችን በማስተዋወቅ ረገድ የተከናወኑትን ሥራዎች ለማስታወስ ይረዳሉ ፡፡ የክርስትና ሃይማኖት አዋቂዎች ፣ የቅዱስ ባስሊዮስል ሥነ ሥርዓት “የታላቁ የቅዱስ ባሲል የግል እጅ ፣ ብዕር ፣ አዕምሮ እና ልብ” ያለአንዳች ስሕተት ያሳያል ። ለእሱ ሊባል የሚችል ሥነ-ስርዓት" የቅዱስ ባስሊዮስል ሥነ-መለኮታዊ ሥነ-ስርዓት)"፣ ብዙ ጊዜ ከተለመዱት ከቅዱስ ዮሐንስ አፍወርቅአገልግሎት የሚረዝም ሥነ-ስርዓት ነው ። በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት ዋናነት ካህኑ በሚያደርገው በጸጥታ ፀሎቱ ላይና ለ ቴዎቶኮስየሚያደርገው ዜማና ቃላት ነው ፣ ‹ፍጥረት ሁሉ› በሚለው ምትክ ፣ ኤክስዮን ኤንቲን የሚለውን የዮሐንስ አፍወርቅን ሥነ-ሥረት ይጠቀማል ። የዮሐንስ አፍወርቅ ሥነ ስርዓት በአብዛኛዎቹ ምስራቃዊው ኦርቶዶክስ እና የባዛንታይን ካቶሊክ ሥነ ሥርዓታዊ ባህሎች ውስጥ የባስሊዮስን ለመተካት መጥቷል ፡፡ ሆኖም ፣ አሁንም በተወሰኑ የበዓላት ቀናት ላይ የባሲል ሥነ-ስርዓት ይጠቀማሉ ፥ የመጀመሪያዎቹ የዐብይ ፆም አምስት እሑዶች ፣ የ ልደት ዋዜማ እና ቴዎናን ፣ በፀሎተ ሐሙስ እና ቅድስት ቅዳሜ እና በጃንዋሪ ፩ የባስሊዮስ ቀን (በ ጁሊያን የቀን መቁጠሪያ የሚከተሉ አብያተ ክርስቲያናት ጄንዋሪ ፲፬ በ የግሪጎሪያን የቀን መቁጠሪያ ላይ ይወድቃል]])። በሞናስቲዝም(ገዳማዊ ኑሮ) ላይ ያለው ተጽዕኖ በእሱ ምሳሌዎች እና ትምህርቶች መሠረት ባስሊዮስል ከዚህ በፊት በምነና ሕግ ማለትም የገዳም ኑሮ ባሕርዪ አመለካከት የነበሩትን ልዩነት ማንንም በማያስቀይም ደረጃ አሻሽሎ አሳይቷል ፡፡ ሁለቱን አጣምሮ የሚይዝ የ ሥራና ፀሎት ቅንጅት ያለው አሠራር በመፍጠሩ ይታወቃል ።
13832
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%A0%E1%88%AD%E1%8D%80%20%E1%8B%B5%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%8D
ሠርፀ ድንግል
ዓፄ ሠርጸ ድንግል ( 1542 - መስከረም 27, 1590 ) በዙፋን ስማቸው "መለክ ሰገድ" ኢትዮጵያን ከ1555 - 1590 ዓ.ም. የመሩ ንጉሥ ነበሩ። አባታቸው ዓፄ ሚናስ ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ እቴጌ አድማስ ሞገስ ነበሩ። ከግራኝ ወረራ ጀምሮ እስከ ዓፄ ሚናስ ዘመን የቀጠለው አለመረጋጋት በኒህ ንጉሥ ዘመን አንጻራዊ እልባት አግኝቷል። ለዚህ ተጠያቂ የሚሆኑ አራት ጉልህ ክስተቶች፡ ፩) በሰሜን የቱርኮች ወረራ በንጉሡ ወታደራዊ ብቃት በመክሸፉ ፪) በደቡብ የባሬንቱ ኦሮሞዎች ሐረርን በመውረራቸው የአዳል ግዛት ኃይል በመዳከሙ እና ስለዚህ ምክንያት ከአዳል ጦርነት በማብቃቱ ፫) የቦረና ኦሮሞዎች ወደ ሸዋ የሚያካሂዱትን ዘመቻ ለጊዜው መግታት በመቻሉ፣ ፬) የአገሪቱን ዋና ከተማ ከመካከለኛው ክፍል ወደ አባይ ምዕራብ በማሻገሩ ነበር። በአጠቃላይ መልኩ ይህ ንጉስ ከሚናስ የተረከበውን ግዛት አስፍቶና አጠናክሮ ለቀጣዩ መሪ ትቶ አልፈዋል። የንግሱ ባለቤት እቴጌ ማርያም ሰናም ለተከታዮቹ ነገሥታት መነሳትም ሆነ መውደቅ ባበረክተችው አስተዋጽኦ በታሪክ ትታወሳለች። ቅድመ መለክ ስገድ በሠርፀ ድንግል የህጻንነት ዘመን የነበረችው አገር ብዙ ውዝግቦችን እምታስተናግድ ነበረች። ከምክንያቶቹ ውስጥ አንደኛው ዓፄ ሚናስ ከፖርቱጋል ካቶሊኮች ጋር አለመስማማቱ ሲሆን ካቶሊኮቹም አንድ ጊዜ ከባህር ንጉስ ይስሐቅ ጋር በማበር ሌላ ጊዜ ባህር ንጉሱ ከቱርኮች ጋር በመተጋገዝ በሚናስ ላይ አመጽና ዘመቻ በመፈጸማቸው ነበር። ሌላው ምክንያት የአዳል ግዛት ኃይሉ እምብዛም ያልተዳከመ ስለነበር በመካከለኛው መንግስት ላይ ጦር የመክፈት ልማዱ አልተገታም ነበር። ሦስተኛው በዘመኑ የአገሪቱ የአስተዳደር ማዕከል የነበረው የሸዋ እና ፈጠገር ክፍሎችን ቦረናዎች መውረር መጀመራችው ነበር። በነዚህ ምክያቶች አገሪቱ በበጋው ወቅት ጦርነት የሚካሄድባት በክረምት ደግሞ ሰፊ ሰራዊት በመያዝ ከጊዜ ወደጊዜ በሚቀያየሩት ዋና ከተሞች የሚሰፈርባት ነበረች። ሠርፀ ድንግል መንገሱ ዓፄ ሚናስ በ1555 ሲሞቱ ቀጣዩ ንጉስን ለመምረጥ የአገሪቱ መሳፍንቶች በሸዋ ተሰበሰቡ። ምንም እንኳ ሠረፀ ድንግል የሚናስ ታላቁ ልጅ ቢሆንም ብዙ ተቀናቃኞች ነበሩት። ከነዚሁም ውስጥ፣ የዓፄ ልብነ ድንግል እህት የወይዘሮ ሮማነወርቅ ልጅ የነበረው ሐመልማል ዋና ሲሆን ሌሎች እንደ ሐርቦ፣ አቤቶ ፋሲል እና ይስሐቅ ያሉ ተገዳዳሪዎች ስብሰባው የተወዛገበ እንዲሆን አድርገውት ነበር። የዚህ ስብሰባ ውጤት የ13 ዓመቱ ሠርፀ ድንግል ንጉስ እንዲሆን ነበር። ሆኖም ሐምልማል ይህን ውጤት ባለመቀበል የጎጃም እና ደምበያ መሳፍንቶችን በማስተባበር በወጣቱ ንጉስ ላይ ዘመቻ ከፍቶ በመጀመሪያ አካባቢ ድል ተቀዳጅቶ ነበር። ይሁንና የቀሳውስቱን እና እንዲሁም እቴጌ ሰብለ ወንጌልን ድጋፍ በማግኘቱ፣ ይህንም ተከትሎ በየጊዜው ቁጥራቸው እየጨመሩ የሄዱ መሳፍንቶችን ከርሱ ጎን በመሰለፋቸው በመጨረሻ ሐመልማልን በጦርነት ለማሸነፍ ቻለ። ጎጃምን ለተሸነፈው ለሐመልማል እንደ ግዛት በመስጠት ሰላም ለማስፈን ቻለ። የአጎቱ ልጆች ማመጽ ይህ ከሆነ በኋላ ባህር ንጉስ ይስሃቅ የተባለው ያሁኑ ኤርትራ መሪ በአጼ ሚናስ ዘመን ያመጸ ቢሆንም ልጁ ሲነግስ የልጁን ስልጣን ተቀበለ። ክሁለት አመት በኋል ፋሲል የተባለው ሌላው ያጎቱ ልጅ አመጽ አስነስተውብታል (ምንም እንኳ ሁቱም ቢሸነፉ)። የቱርኮች ጦርነት፣ የግንቦች መታነጽ ፣ በአክሱም የአክሊል መድፋት መልሶም በ1569 ከቱርኮች ጋር ባደረገው ጦርነት ለመጀመሪያ ጊዜ ቱርኮችን አሸነፈ። ለዚህ መታሰቢያ በእምፍራዝ (ጉዛራ) በ1571 ቤ/መንግስት አሰራ። ወደ ሰሜንም በመዝለቅ በወገራ እና በአይባ ሌሎች ቤ/መንግስቶችን አሰርቷል። የኪዳነ ምህርት ቤ/ክርስቲያንም እንዲሁ። ከዚያም ባህር ንጉስ ይስሐቅ በኦቶማን ቱርኮችና በአዳል ሰራዊት ታግዞ አመጽ ማስነሳቱ አልቀረም። በዚህ ጊዜ ንጉሱ ወደ ትግራይ በመዝመት በ1578 ባህረ ነጋሹንና (በአዲ ቆሮ) አባሪ ኦቶማኑን ኦዝደሚር ፓሻንና የአዳል መሪ የነበረውን ሱልጣን መሃመድ አራተኛ (በተምቤን) ጦርነት አሸንፎ ገደላቸው። በድባርዋ (የድሮው ኤርትራ ዋና ከተማ) የነበሩት ቱርኮችም ያለምንም ተኩስ እጃቸውን ሰጡ። በዚያውም ሰርጸ ድንግል በአክሱም ስርዓተ ተክሊሉን ፈጸመ (ይህ እንግዲህ ከዘርዓ ያዕቆብ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ነው)፣ መልአክ ሰገድ የሚለውንም ስም ያገኘው በዚህ ጊዜ ነበር። ከ10 አመት በሁዋላ፣ በ1588 ኦቶማን ቱርኮች፣ ከተባረሩበት ድባርዋ መልሰው ሊቆጣጠሩ ሲሞክሩ በመሸነፋቸው አርቂቆ ላይ የነበረውን ግዛታቸውን ሰርጸ ድንግል አፈረሰባቸው። በዚህ ምክንያት የቱርኩ መሪ ፓሻ በወርቅ ያጌጠ ፈረስ እስከ ሳዱላው በመላክ ከንጉሱ ዘንድ ሰላም እንደሚሻ አስታወቀ። ሌሎች ዘመቻዎች እና ሰላም ሰርጸ ድንግል የኖረበት ዘመን ከግራኝ አህመድ ወረራ ጥቂት ዘመን አሳልፎ ስለነበር የህዝቦች ፍልሰት በዚሁ ዘመን ይታይ ነበር። የኦሮሞን ወደ ሰሜን ወረራ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋፈጠ ንጉስ ይሄው ሰርጸ ድንግል ነው። በዚሁ ዘመን የኦሮሞወች ጥንካሬ ከማየሉ የተነሳ ኑር ኢብን ሙጃሂድ የተሰኘውን የግራኝን ምትክ በመግደል ሐረርን ወረው ነበር። ቀጥሎም ወደሰሜን በመዝመት ሰርጸ ድንግል በነገሰ በ10ኛው አመት ዝዋይ ሃይቅ አካባቢ ከንጉሱ ሰራዊት ጋር ተጋጭተው ተሸነፉ። ከዚህ በኋላ ንጉሱ በኦሮሞወች ቡድኖች ላይ በ1578 እና በ1588 ዘምቷል። በ1580 እና 85 ደግሞ በቤተ እስራኤል (ፈላሾች) ቡድኖች ላይ ዘምቷአል። አገው ላይም በ1581 እና 85፣ ጋምቦ ላይ በ 1590 እናም ሱዳን ውስጥ በሻንቅላ ላይ አድርጓል። እንራያ ደግሞ ሁለት ጊዜ በ 1586 እና 97 ጦርነት በመክፍት ህዝቡን ከነመሪያቸው ክርስቲያን አደርገ። ስለመጨረሻው የ1597 ዓ.ም. ዘመቻው የንጉሱ ዜና-መዋዕል እንዲህ ሲል ያትታል፡ መነኮሳት ተሰብስበው ንጉሱ ወደዳሞት ጦር ሜዳ እንዳይሄድ ለመኑት፣ ንጉሱ ግን ልቡ እንደደነደነ ስለተገነዘቡ በተወሰነ ወንዝ [አሳ የሚበዛበት የገሊላ ወንዝ ] ውስጥ የሚገኝን አሳ እንዳይበላ አጥብቀው አስጠነቀቁት። እሱ ግን የተባለውን ቸል በማለት ባስጠነቀቁት ወንዝ ሲያልፍ ከዚይ ወንዝ የወጣን አሳ በላ። ሳይዘገይም በጸና ታመመና ሞተ። በሞተም ጊዜ ሬማ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ፣ መድሃኔ አለም ቤ/ክርስቲያን ተቀበረ። የሰርጸ ድንግል መንግስት ረጅምና ከመጀመሪያው ጀምሮ ብዙ ጦርነት የበዛበት ቢሆንም ንጉሱ ለልጁ ያዕቆብ ያስረከበው ግዛት ግን ሰላማዊና ያልተከፋፈለ ታላቅ ሃገር ነበር። የስልጣን ሽግግር በጥንቱ ኢትዮጵያ ታሪክ የስልጣን ሽግግር ብዙ ችግር የተሞላበት ነበር። የሰርጸ ድንግል ስርዓትም ከዚህ አላመለጠም። አጼ ሰርጸ ድንግል ከህጋዊ ባለቤታቸው ንግስት ማርያም ሰና ሴት ልጆችን እንጂ ወንድ ልጅ አላገኙም። ሐረግዋ ከተባለች የቤተ እስራኤል (ፈላሻ) ቅምጣቸው ግን ያዕቆብ የሚባል ወንድ ልጅ ነበራቸው። ይሁንና ልጅ አባቱ በሞተ ጊዜ ገና የ7 አመት ህጻን ነበር። በዚህ ምክንያት የሰርጸ ድንግል ወንድም ልጅ የነበረው ዘድንግል ስልጣን ላይ ይወጣል የሚል ግምት በመላ ሃገሪቱ ተንሰራፍቶ ነበር። ነገር ግን ንግስት ማርያም ሰና ከልጆቻ ባለቤቶች ራስ አትናትዮስ የጎንደር መሪ እና ራስ ክፍለ ዋህድ የትግራይ መሪ ጋር በመሆን ህጻኑን የእንጀራ ልጇን ያዕቆብን በራስ አትናቲዮስ ሞግዚትነት የንጉሰ ነገስትነቱን ስልጣን እንዲወርስ አደረገች። ዋቢ መጻሕፍት ሠርፀ ድንግል የኢትዮጵያ ነገሥታት
11831
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B1%E1%88%AD%E1%8A%AD
ቱርክ
ቱርክ አገር (ቱርክኛ፦ /ቲውርኪየ/) ወይም የቱርክ ሬፑብሊክ ( /ቲውርኪየ ጁምሁሪየትዕ) በእስያና በአውሮፓ አሳላጭ ድንበር መሀል የምትገኝ ሀገር ናት። ዋና ከተማዋም አንካራ ሲሆን ኢስታንቡል ደግሞ ትልቁን የንግድ፣ የባህልና፣ የአስተዳደር ማዕከል ነው። ጥንታዊቷ ቱርክ የብዙ የኒዮሊቲክ ስልጣኔ መዳረሻ ስትሆን፣ የሃቲ ህዝቦች፣ የሚሲኒያን ግሪክ እንዲሁም የአናቶሊያ ህዝቦች ይኖሩባት ነበር። በግሪክ ዘመን ከታላቁ እስክንድር ቅኝ ግዛት ጀምሮ፣ የቱርክ ጥንታዊ ከተሞች የግሪክ ባህል እንዲኖራቸው አድርጓል። ይህም በቢዛንታይን ዘመን እንደቀጠለ ቆይቷል። በቢዛንታይን ዘመን፣ ቱርክ ዋና መናከሻ ስትሆን ዋና ከተማዋም "ኮንስታንቲኖፕል" (የአሁኗ ኢስታንቡል) ነበር። የሴልጁክ ቱርክ አናቶሊያን እስከ 1243 ሞንጎል ወረራ ድረስ ሲመራ ከዛ በኋላ የቱርክ ክልሎች መገነጣጠል ጀመሩ። በ13ተኛው ክፍለ ዘመን የኦቶማን ግዛት የባልካን ክፍሎችን በመግዛት የቱርክ ሀያልነት እንዲመጣ አድርገዋል። ማህመድ ሁለተኛው ኮንስታንቲኖፕልን በ1453 ዓም ሲገዛ የሰሊም ንግስና ኦተማኖች ድንበራቸው እንዲለጠጥ አድርጓል። ይህም እስከ 18ተኛው ክፍለ ዘመን ድርስ ነበር። ነገር ግን በማህሙድ ሁለተኛው አማካኝነት ኦቶማን ቱርክ ልታድግና ልዘምን ችላለች። "ያንግ ቱርክ ሪቮሊውዥን" የተባለው ጊዜ የኦቶማን መንግስት በሱልጣን እንዳትመራና ወደ ፓርቲ ተወዳዳሪነት ዘዴ እንድትለወጥ አድርጓል። የ1913ቱ መፈንቅለ መንግሥት ኦቶማን ቱርክ በሶስት ፓሻዎች እንድትመራ አድርጎል። ይህም አስተዳደር ኦቶማኖች ወደ አንደኛው የአለም ጦርነት እንድትገባ አድርጎል። ኦቶማን በጦርነቱ ላይ በአርመን፣ በግሪክ፣ እና በአሱሪያውያን ህዝቦች ላይ አሰቃቂ የዘር ጭፍጨፋ አድርጋለች። ልክ ኦቶማን እንደተሸነፈች፣ በ1922 ዓም መፍረስ ጀመረች። ይህም ግዛቷ በአላይድ ፓወር በመያዝ፣ የአሁኗ ቱርክ ከብዙ ጥረት መመስረት ቻለች። ከዛ ጊዜ በኋላ ቱርክ ወደ ሪፐብሊክ ተቀየረች። ቱርክ በ1952 ዓም የኔቶ አባል መሆን ጀመረች። ቱርክ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ የፖለቲካና የኑሮ ቅውስነት ደርሶባታል። በ2017 ዓም ቱርክ በህዝብ ውሳኔ አማክኝነት ከፓርላማ ወደ ፕሬዚዳንት አመራር ዘዴ ተለውጣለች። የአሁኑ ፕሮዚዳንቷ ሬሴፕ ታይፕ ኤርዶጋን በብዙ ሀያሲያን አምባገነናዊና እስላማዊ አገዛዝ አለው ይባላል። በተጨማሪም፣ ሀገሪቱን ለትልቅ የገንዘብና የምጣኔ ሀብት ቀውስ ውስጥ ሊከታት ችሏል ይላሉ። ቱርክ ሀያላን ሀገር ናት። እንዲሁም በኢንዱስትሪ የበለፀገችም ናት። የቱርክ ጊዜአት እንደ ኦቶማን መንግስት ምዕራባውያን መር አምባገነናዊ የአለም መንግስት (ኒው ወርልድ ኦርደር) ለማምጣት ፈር ቀዳጅ ነበረች። የቱርክን ልሳነ ድምፅ ሆና የተነሳችው ይህች ግዛት፣ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ላይ ባደረገችው የአርመን ጭፍጨፋ ፀረ ክርስትና እንደሆነ የታወቀ ነገር ነው። የአሁኗ ቱርክ የተወሰኑትን የምዕራብያውያን ሀሳቦችን በመኮረጅ በአንፃራዊ ዌስተርናይዝድ የሆነች ናት። የቱርክ አቋም ባይገመትም የአውሮፓ ህብረትን ለመቀላቀልና ዝግጁ እንደሆነች ቆይታለች። የቱርክ ህዝቦች ጣልቃ ገብነት የሚቃወሙ ባህል ተኮር እሴት ያላቸው ናቸው። የቱርክ የነጻነት ጦርነት በህዳር 1 ቀን 1922 የሱልጣኔቱን መጥፋት ፣ የላውዛን ስምምነት (የሴቭሬስ ስምምነትን የተተካ) በጁላይ 24 ቀን 1923 እና የሪፐብሊኩ አዋጅ በጥቅምት 29 ቀን 1922 ተፈርሟል። 1923. በሀገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት ሙስጠፋ ከማል አታቱርክ በተጀመረው ማሻሻያ ቱርክ ሴኩላር ፣ አሃዳዊ እና ፓርላማ ሪፐብሊክ ሆነች። ቱርክ በኮሪያ ጦርነት ውስጥ ትልቅ ሚና ተጫውታለች እና በ1952 ኔቶን ተቀላቀለች። ሀገሪቱ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ አጋማሽ ላይ በርካታ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስቶችን አሳልፋለች። እ.ኤ.አ. በ1980ዎቹ ኢኮኖሚው ሊበራላይዝድ ተደረገ፣ ይህም ወደ ጠንካራ የኢኮኖሚ እድገት እና የፖለቲካ መረጋጋት አመራ። የፓርላማው ሪፐብሊክ እ.ኤ.አ. በ 2017 በፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በፕሬዝዳንታዊ ስርዓት ተተካ ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አዲሱ የቱርክ መንግስት በፕሬዚዳንት ሬሴፕ ጣይብ ኤርዶጋን እና ፓርቲያቸው ኤኬፒ ብዙ ጊዜ እስላማዊ እና አምባገነን እንደሆኑ ይገለጻል። የኋለኛው በሀገሪቱ ላይ ያለው አገዛዝም በርካታ የገንዘብ ቀውሶችን አስከትሏል፣ የዋጋ ግሽበት እና የኢኮኖሚ ውድቀት፣ እንዲሁም የድህነት መጨመርን አስከትሏል። ቱርክ የክልል ሃይል እና አዲስ በኢንዱስትሪ የበለፀገች ሀገር ነች ፣ጂኦፖለቲካዊ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ ያላት ሀገር ነች። በማደግ ላይ ካሉ እና በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች መካከል የተከፋፈለው ኢኮኖሚ፣ በስመ ከአለም 20ኛ-ትልቁ፣ እና በፒፒፒ አስራ አንደኛው-ትልቅ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር አባል፣ የኔቶ አባል፣ አይኤምኤፍ እና የአለም ባንክ የቀድሞ አባል እና የኦኢሲዲ፣ ኦኤስሲኢ፣ ቢኤስኢሲ፣ ኦአይሲ እና ጂ20 መስራች አባል ነው። እ.ኤ.አ. የአናቶሊያን ባሕረ ገብ መሬት፣ አብዛኛው ዘመናዊ ቱርክን ያቀፈው፣ በዓለም ላይ ካሉት በጣም ጥንታዊ በቋሚነት የሰፈሩ ክልሎች አንዱ ነው። የተለያዩ ጥንታዊ አናቶሊያውያን ህዝቦች በአናቶሊያ ውስጥ ኖረዋል፣ ቢያንስ ከኒዮሊቲክ እስከ ሄለናዊው ዘመን ድረስ። ከእነዚህ ህዝቦች ውስጥ ብዙዎቹ የአናቶሊያን ቋንቋዎች ይናገሩ ነበር, የትልቁ ኢንዶ-አውሮፓ ቋንቋ ቤተሰብ ቅርንጫፍ ነው, እና የኢንዶ-አውሮፓዊ ሂትያን እና የሉዊያን ቋንቋዎች ጥንታዊነት ግምት ውስጥ በማስገባት አንዳንድ ሊቃውንት አናቶሊያን ኢንዶ-አውሮፓዊ ከሚገኝበት መላምታዊ ማዕከል አድርገው አቅርበዋል. ቋንቋዎች ተበራከቱ። የቱርክ የአውሮፓ ክፍል፣ ምስራቃዊ ትሬስ ተብሎ የሚጠራው፣ እንዲሁም ቢያንስ ከአርባ ሺህ ዓመታት በፊት ጀምሮ ይኖሩ ነበር፣ እና በኒዮሊቲክ ዘመን በ6000 ዓክልበ ገደማ እንደነበረ ይታወቃል። ጎቤክሊ ቴፒ እጅግ ጥንታዊው ሰው ሰራሽ የሃይማኖት መዋቅር የሚገኝበት ቦታ ሲሆን በሺህ ለሚቆጠሩ ዓመታት የቆየ ቤተ መቅደስ ሲሆን ቻታልሆይዩክ በደቡባዊ አናቶሊያ ውስጥ በጣም ትልቅ የኒዮሊቲክ እና የቻልኮሊቲክ ሰፈር ሲሆን ይህም በግምት ከ 5700 ዓክልበ. ገደማ ነበር። እስከዛሬ የተገኘ ትልቁ እና በይበልጥ የተጠበቀው የኒዮሊቲክ ቦታ ሲሆን የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ነው። ኔቫሊ ቾሪ በመካከለኛው ኤፍራጥስ ላይ በሻንሊዩርፋ ውስጥ ቀደምት የኒዮሊቲክ ሰፈር ነበር። የኡርፋ ሰው ሐውልት ቀኑ ሐ. ከክርስቶስ ልደት በፊት ባሉት ሁለት ሺህ ዓመታት በፊት እስከ ቅድመ-የሸክላ ኒዮሊቲክ ዘመን ድረስ ፣ እና እንደ “የሰው ልጅ እጅግ ጥንታዊ የተፈጥሮ የተፈጥሮ ሕይወት-መጠን ቅርፃቅርፅ” ተደርጎ ይቆጠራል። ከጎቤክሊ ቴፔ ጣቢያዎች ጋር እንደ ወቅታዊ ተደርጎ ይቆጠራል። የትሮይ ሰፈራ በኒዮሊቲክ ዘመን ተጀምሮ እስከ የብረት ዘመን ቀጠለቀደምት የተመዘገቡት የአናቶሊያ ነዋሪዎች ሃቲያውያን እና ሑራውያን፣ ኢንዶ-አውሮፓውያን ያልሆኑ ኢንዶ-አውሮፓውያን ሕዝቦች በመካከለኛው እና በምስራቅ አናቶሊያ ይኖሩ ነበር፣ በቅደም ተከተል፣ እንደ መጀመሪያ ሐ. 2300 ዓክልበ. ኢንዶ-አውሮፓውያን ኬጢያውያን ወደ አናቶሊያ መጡ እና ቀስ በቀስ ሃቲያንን እና ሁሪያንን ያዙ። 2000-1700 ዓክልበ. በአካባቢው የመጀመሪያው ትልቅ ግዛት የተመሰረተው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ18ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በኬጢያውያን ነው። አሦራውያን ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1950 ዓክልበ. እስከ 612 ዓክልበ ድረስ በደቡብ ምስራቅ ቱርክ አንዳንድ ቦታዎችን ድል አድርገው ሰፈሩ፣ ምንም እንኳን በአካባቢው አናሳ ሆነው ቢቆዩም፣ ማለትም በሃካሪ፣ እና ማርዲን። ኡራርቱ በ9ኛው ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በአሦራውያን ጽሑፎች ውስጥ እንደ ኃይለኛ ሰሜናዊ የአሦር ተቀናቃኝ ሆኖ እንደገና ብቅ አለ። የኬጢያውያን ግዛት መፍረስን ተከትሎ ሐ. 1180 ዓክልበ. ፍሪጂያውያን፣ ኢንዶ-አውሮፓውያን፣ በ7ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ መንግሥታቸው በሲሜሪያውያን እስኪጠፋ ድረስ በአናቶሊያ ወደ ላይ ከፍ ብለው መጡ። ከ 714 ዓክልበ ጀምሮ፣ ኡራርቱ ተመሳሳይ እጣ ፈንታ ተካፍላለች እና በ590 ዓክልበ. በሜዶን በተወረረች ጊዜ ሟሟት። ከፍርግያ ተተኪ ግዛቶች መካከል በጣም ኃይለኛ የሆኑት ሊዲያ፣ ካሪያ እና ሊሺያ ነበሩ። ሰርዴስ በምእራብ ቱርክ ዘመናዊ ሰርት የሚገኝበት ጥንታዊ ከተማ ነበረች። ከተማዋ የጥንቷ የልድያ መንግሥት ዋና ከተማ ሆና አገልግላለች። በእስያ ካሉት ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ እንደመሆኑ መጠን፣ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በራእይ መጽሐፍ ውስጥ፣ የልድያ አንበሳ ሳንቲሞች ከኤሌክትረም የተሠሩ ነበሩ፣ በተፈጥሮ የተገኘው የወርቅ እና የብር ቅይጥ ግን ተለዋዋጭ የከበረ ብረት ዋጋ ያለው ነው። በንጉሥ ክሪሰስ የግዛት ዘመን የሰርዴስ ሜታላሪስቶች ወርቅን ከብር የመለየት ምስጢር በማግኘታቸው ከዚህ በፊት የማይታወቁ የንጽህና ብረቶች ሆኑ። ከ1200 ዓክልበ. አካባቢ ጀምሮ፣ የአናቶሊያ የባህር ዳርቻ በኤኦሊያን እና በአዮኒያ ግሪኮች በብዛት ይሰፍራል። በእነዚህ ቅኝ ገዢዎች እንደ ዲዲማ፣ ሚሌተስ፣ ኤፌሶን፣ ሰምርና (አሁን ኢዝሚር) እና ባይዛንቲየም (አሁን ኢስታንቡል) በመሳሰሉት ቅኝ ገዥዎች በርካታ አስፈላጊ ከተሞች ተመስርተዋል፣ የኋለኛው በግሪክ ቅኝ ገዥዎች ከሜጋራ በ657 ዓክልበ. የተመሰረተው ከቅድመ-ሶቅራታዊ ፈላስፋዎች መካከል አንዳንዶቹ በጣም ታዋቂ ነበሩ። በሚሊጢን ከተማ ኖረ። ታሌስ ኦቭ ሚሌተስ (በ624 ዓክልበ - 546 ዓክልበ. ግድም) በግሪክ ወግ እንደ መጀመሪያ ፈላስፋ ተቆጥሯል። እሱ በሌላ መልኩ በሳይንሳዊ ፍልስፍና እንደተዝናና እና እንደተሳተፈ የሚታወቅ የመጀመሪያው ግለሰብ እንደሆነ በታሪክ ይታወቃል። በሚሊተስ፣ እሱ ቀጥሎ ሁለት ጉልህ ቅድመ-ሶቅራታዊ ፈላስፎች አናክሲማንደር (610 ዓክልበ - 546 ዓክልበ. ግድም) እና አናክሲሜኔስ (እ.ኤ.አ. 585 ዓክልበ - 525 ዓክልበ) (በአጠቃላይ ለዘመናዊ ሊቃውንት የሚሊሲያን ትምህርት ቤት በመባል ይታወቃል)።ታላቁ ፋርስ ግሪክን ከመውረሩ በፊት ለብዙ መቶ ዓመታት ምናልባትም የግሪክ ዓለም ታላቅ እና ባለጸጋ ከተማ ሚሊተስ ነበረች እና ከማንኛውም የግሪክ ከተማ የበለጠ ብዙ ቅኝ ግዛቶችን መሰረተች። በተለይም በጥቁር ባህር አካባቢ. በ 412 በአናቶሊያ ጥቁር ባህር ዳርቻ በምትገኘው በአዮኒያ ቅኝ ግዛቶች ውስጥ በአንዱ ሲኖፔ የተወለደው የሲኒክ ፍልስፍና መስራቾች መካከል ዲዮጋን ዘ ሲኒክ አንዱ ነው። የትሮይ ጦርነት የተካሄደው በጥንቷ ትሮይ ከተማ በአቻውያን (ግሪኮች) የፓሪስ ትሮይ ሄለንን ከባለቤቷ ሚኒላውስ ከስፓርታ ንጉስ ከወሰደች በኋላ ነው። ጦርነቱ በግሪክ አፈ ታሪክ ውስጥ በጣም አስፈላጊ ከሆኑት ክንውኖች አንዱ ነው እና በብዙ የግሪክ ሥነ-ጽሑፍ ሥራዎች በተለይም በሆሜር ኢሊያድ የተተረከ ነው። ከትሮጃን ጦርነት ጀርባ ምንም አይነት ታሪካዊ እውነታ አለ ወይ የሚለው ግልጽ ጥያቄ ነው። የትሮጃን ጦርነት ታሪክ ከተለየ ታሪካዊ ግጭት የተወረሰ ነው ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ12ኛው ወይም በ11ኛው ክፍለ ዘመን ነበር፣ ብዙ ጊዜ በኤራቶስቴንስ ከ1194-1184 ዓክልበ. የሰጡትን ቀኖች ይመርጣሉ፣ ይህም ለአደጋ ከአርኪኦሎጂያዊ ማስረጃዎች ጋር ይዛመዳል። የትሮይ ማቃጠል እና የኋለኛው የነሐስ ዘመን ውድቀት። በአጎራባች ህዝቦች አርመኒያ ተብሎ የሚጠራው የመጀመሪያው ግዛት የአርሜኒያ ኦሮንቲድ ሥርወ መንግሥት ግዛት ሲሆን ይህም ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ6ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ አሁን ምስራቃዊ ቱርክ ያለውን ክፍል ያካትታል። በሰሜን ምዕራብ ቱርክ፣ በታሬስ ውስጥ በጣም አስፈላጊው የጎሳ ቡድን በቴሬስ የተመሰረተው ኦዲሪሲያን ነው። የዛሬዋ ቱርክ በሙሉ በፋርስ አቻምኒድ ኢምፓየር በ6ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. የግሪክ-ፋርስ ጦርነት የጀመረው በአናቶሊያ የባህር ዳርቻ ላይ ያሉ የግሪክ ከተማ ግዛቶች በፋርስ አገዛዝ ላይ በ499 ዓክልበ.የካሪያ ቀዳማዊ አርጤሜስያ የጥንቷ ግሪክ ከተማ-ሃሊካርናሰስ ንግሥት ነበረች እና በሁለተኛው የፋርስ የግሪክ ወረራ ወቅት የፋርስ ንጉሥ ቀዳማዊ ጠረክሲስ አጋር በመሆን ከግሪክ ከተማ ግዛቶች ጋር ተዋግታለች። በ 480 ዓክልበ. በ480 ዓክልበ በአርጤምሲየም የባህር ኃይል ጦርነት ላይ የአምስት መርከቦችን አስተዋፅዖ በግሏ አዘዘች። በኋላም የቱርክ ግዛት በ334 ዓክልበ በታላቁ አሌክሳንደር እጅ ወደቀ፣ይህም በአካባቢው የባህል ተመሳሳይነት እና ሄሌኒናይዜሽን እንዲጨምር አድርጓል። በ323 ዓክልበ እስክንድር መሞትን ተከትሎ አናቶሊያ በመቀጠል ወደ ተለያዩ ትናንሽ የሄለናዊ መንግስታት ተከፋፈለ፣ እነዚህም ሁሉም የሮማ ሪፐብሊክ አካል የሆነው በ1ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ነው። በአሌክሳንደር ወረራ የጀመረው የሄሌኔዜሽን ሂደት በሮማውያን አገዛዝ እየተፋጠነ ሄደ፣ እና በክርስትና ዘመን መጀመሪያዎቹ መቶ ዓመታት አካባቢ የአናቶሊያ ቋንቋዎች እና ባህሎች ጠፍተዋል፣ በአብዛኛው በጥንታዊ ግሪክ ቋንቋ እና ባህል ተተኩ። ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ 3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ የዘመናዊቷ ቱርክ ትላልቅ ክፍሎች በሮማውያን እና በአጎራባች ፓርቲያውያን መካከል በሮማውያን እና በፓርቲያውያን ጦርነቶች መካከል ተፋጠዋል። ገላትያ በማዕከላዊ አናቶሊያ ደጋማ ቦታዎች ኬልቶች ይኖሩበት የነበረ ጥንታዊ ቦታ ነው። “ገላትያ” የሚሉት ቃላት በግሪኮች ለሦስቱ የሴልቲክ ሕዝቦች አናቶሊያ ይጠቀሙ ነበር፡- ፣ እና ። ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1ኛው ክፍለ ዘመን ኬልቶች በጣም ግሪካዊ ስለነበሩ አንዳንድ የግሪክ ጸሐፊዎች ሄሌኖጋላታይ () ብለው ይጠሯቸው ነበር። ገላትያ የተሰየመው በጋውልስ ከትሬስ (ቲሊስ) በተባለው ስም ነው፣ እዚህ ሰፈሩ እና በ 3 ኛው ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት ትንሽ ጊዜያዊ የውጭ ጎሳ ሆነ፣ በ279 ዓክልበ የባልካንን የጋሊኮች ወረራ ተከትሎ። የጰንጦስ መንግሥት የሄለናዊ መንግሥት ነበር፣ በጶንጦስ ታሪካዊ ክልል ላይ ያተኮረ እና በፋርስ አመጣጥ በሚትሪዳቲክ ሥርወ መንግሥት የሚመራ፣ እሱም ከታላቁ ዳርዮስ እና ከአካሜኒድ ሥርወ መንግሥት ጋር በቀጥታ የተያያዘ ሊሆን ይችላል። መንግሥቱ በ281 ዓክልበ. በሚትሪዳተስ 1 የታወጀ ሲሆን በ63 ዓክልበ. በሮማ ሪፐብሊክ እስከ ድል ድረስ ዘልቋል። የጰንጦስ መንግሥት በታላቁ በሚትሪዳተስ ታላቅ ደረጃ ላይ ደርሷል፣ እሱም ኮልቺስን፣ ቀጰዶቅያን፣ ቢቲኒያን፣ የቱሪክ ቼርሶኔሶስ የግሪክ ቅኝ ግዛቶችን ድል አደረገ። በሚትሪዳቲክ ጦርነቶች ከሮም ጋር ከረዥም ጊዜ ትግል በኋላ ጶንጦስ ተሸነፈ። ከዘመናዊቷ ቱርክ ጋር የሚዛመዱ ሁሉም ግዛቶች በመጨረሻ በሮማ ኢምፓየር ቁጥጥር ስር ወድቀዋል። የጥንት የክርስትና እና የሮማውያን ዘመን በሐዋርያት ሥራ መሠረት፣ በደቡባዊ ቱርክ የምትገኝ አንጾኪያ (አሁን አንታክያ) የኢየሱስ ተከታዮች ለመጀመሪያ ጊዜ “ክርስቲያኖች” ተብለው የተጠሩባትና በፍጥነት የክርስትና አስፈላጊ ማዕከል ሆናለች።[ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ኤፌሶን ሄዶ በዚያ ቆየ። በቆሮንቶስ በቆየ ጊዜ እንዳደረገው ለሦስት ዓመታት ያህል ምናልባትም በዚያ ድንኳን ሠሪ ሆኖ እየሠራ ነበር። ብዙ ተአምራትን እንዳደረገ፣ ሰዎችን እየፈወሰና አጋንንትን እንደሚያወጣ ይነገርለታል፤ እንዲሁም በሌሎች ክልሎች የሚስዮናውያንን ሥራ እንዳደራጀም ግልጽ ነው። የባይዛንታይን ጊዜ በ324፣ ቀዳማዊ ቆስጠንጢኖስ አዲስ የሮም ግዛት ዋና ከተማ እንድትሆን ቤዛንቲየምን መረጠ። በቆስጠንጢኖስ ዘመን፣ ክርስትና የመንግሥት ሃይማኖት ብቻ አልነበረም፣ ነገር ግን በንጉሠ ነገሥት ምርጫ ተደስተው ነበር፣ ምክንያቱም በበጎ መብት ይደግፈው ነበር። በ395 የቴዎዶስዮስ 1ኛ ሞት እና የሮማን ኢምፓየር በሁለቱ ልጆቹ መካከል ቋሚ ክፍፍል ከተፈጠረ በኋላ፣ በሕዝብ ዘንድ ቁስጥንጥንያ እየተባለ ትጠራ የነበረችው ከተማ የምስራቅ ሮማን ኢምፓየር ዋና ከተማ ሆነች። በኋላ ላይ የባይዛንታይን ኢምፓየር ተብሎ የሚጠራው ይህ ኢምፓየር አብዛኛው የአሁኗ ቱርክ ግዛት እስከ መካከለኛው ዘመን መገባደጃ ድረስ ይገዛ ነበር። ምንም እንኳን የምስራቃዊ ክልሎች እስከ 7 ኛው ክፍለ ዘመን እዘአ የመጀመሪያ አጋማሽ ድረስ በሳሳኒያውያን እጅ ጸንተው ቢቆዩም። ለዘመናት የዘለቀው የሮማን ፋርስ ጦርነቶች ቀጣይ የባይዛንታይን-ሳሳኒድ ጦርነቶች በዛሬዋ ቱርክ በ4ኛው እና በ7ኛው መቶ ዘመን እዘአ መካከል በተለያዩ ቦታዎች ተካሂደዋል። በ325 የኒቂያ (ኢዝኒክ) የመጀመሪያው ምክር ቤት፣ የመጀመሪያው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ (ኢስታንቡል) በ381፣ የኤፌሶን ጉባኤ በ431 እና ምክር ቤትን ጨምሮ በዛሬዋ ቱርክ ውስጥ በሚገኙ ከተሞች ውስጥ በርካታ የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን ጉባኤዎች ተካሂደዋል። የኬልቄዶን (ካዲኮይ) በ 451 እ.ኤ.አ ሴልጁክስ እና የኦቶማን ኢምፓየር የሴልጁክ ቤት በ9ኛው ክፍለ ዘመን ከካስፒያን እና ከአራል ባህር በስተሰሜን በሚገኘው በያብጉ ካጋኔት ኦግኡዝ ኮንፌደሬሽን በሙስሊም አለም ዳርቻ ከሚኖሩ የኦጉዝ ቱርኮች የኪኒክ ቅርንጫፍ የተገኘ ነው። በ10ኛው ክፍለ ዘመን። ምዕተ-አመት፣ ሴልጁኮች ከቅድመ አያቶቻቸው ወደ ፋርስ መሰደድ ጀመሩ፣ እሱም በቱሪል ከተመሰረተ በኋላ የታላቁ ሴልጁክ ኢምፓየር አስተዳደራዊ እምብርት ሆነ። በ 11 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ አጋማሽ ላይ የሴልጁክ ቱርኮች ወደ መካከለኛው ዘመን አርሜኒያ እና አናቶሊያ ምስራቃዊ ክልሎች ዘልቀው መግባት ጀመሩ። እ.ኤ.አ. በ 1071 ሴልጁክስ በአካባቢው የቱርክን ሂደት በመጀመር በማንዚከርት ጦርነት ላይ የባይዛንታይንን ድል አደረጉ ። የቱርክ ቋንቋ እና እስልምና ከአርሜኒያ እና አናቶሊያ ጋር ተዋወቁ, ቀስ በቀስ በመላው ክልሉ ተሰራጭቷል. በአብዛኛው ክርስቲያን እና ግሪክኛ ተናጋሪ ከሆነው አናቶሊያ ወደ አብላጫ ሙስሊም እና ቱርክኛ ተናጋሪዎች የተደረገው አዝጋሚ ሽግግር በመካሄድ ላይ ነበር። በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኮንያ በሱፊ ገጣሚ ሴላዲን ሩሚ የተቋቋመው የሜቭሌቪ የደርቪሾች ትዕዛዝ ቀደም ሲል ሄሌኒዝድ የነበሩትን የአናቶሊያን የተለያዩ ህዝቦች እስላም ለማድረግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ስለዚህ፣ ከግዛቱ ቱርኪፊኬሽን ጎን ለጎን፣ በባህል የፋርስ እምነት ተከታዮች የሆኑት ሴልጁኮች በአናቶሊያ ውስጥ የቱርኮ-ፋርስ ዋና ባህልን መሠረት ያደረጉ ሲሆን በመጨረሻም ተተኪዎቻቸው ኦቶማኖች ይረከባሉ። እ.ኤ.አ. በ 1243 የሴልጁክ ጦር በሞንጎሊያውያን በኮሴ ዳግ ጦርነት በመሸነፉ የሴልጁክ ኢምፓየር ኃይል ቀስ በቀስ እንዲበታተን አደረገ። በቀዳማዊ ዑስማን ከሚመራው የቱርክ ርእሰ መስተዳድር አንዱ በሚቀጥሉት 200 ዓመታት ወደ ኦቶማን ኢምፓየር ይለወጣል። ኦቶማኖች የባይዛንታይን ኢምፓየር ወረራቸዉን ያጠናቀቁት ዋና ከተማዋን ቁስጥንጥንያ በ1453 በመያዝ ነበር፡ አዛዣቸዉ ከዚያ ወዲያ መህመድ አሸናፊ በመባል ይታወቃል። በ1514 ሱልጣን ሰሊም 1ኛ የሳፋቪድ ሥርወ መንግሥት ሻህ እስማኤልን በቻልዲራን ጦርነት በማሸነፍ የግዛቱን ደቡባዊ እና ምስራቃዊ ድንበሮች በተሳካ ሁኔታ አስፋፍቷል። እ.ኤ.አ. በ 1517 ሰሊም 1 የኦቶማን አገዛዝ ወደ አልጄሪያ እና ግብፅ አስፋፍቷል እና በቀይ ባህር ውስጥ የባህር ኃይል መገኘትን ፈጠረ ። በመቀጠልም በኦቶማን እና በፖርቱጋል ግዛቶች መካከል በህንድ ውቅያኖስ ውስጥ የበላይ የባህር ሃይል ለመሆን ፉክክር ተጀመረ ፣በቀይ ባህር ፣በአረብ ባህር እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ ላይ በርካታ የባህር ሃይል ጦርነቶች ተካሂደዋል። በህንድ ውቅያኖስ ውስጥ የፖርቹጋሎች መገኘት የኦቶማን ሞኖፖሊ በምስራቅ እስያ እና በምዕራብ አውሮፓ መካከል ባለው ጥንታዊ የንግድ መስመሮች ላይ ስጋት እንደሆነ ተገንዝቧል። በአውሮፓ ታዋቂነት እየጨመረ ቢመጣም የኦቶማን ኢምፓየር ከምስራቅ ጋር የነበረው የንግድ ልውውጥ እስከ 18ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛ አጋማሽ ድረስ እያደገ ሄደ። በ16ኛው እና በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኦቶማን ኢምፓየር ሃይል እና ክብር ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፣በተለይ በሱለይማን ግርማዊ መንግስት ዘመን፣ እሱም በግላቸው በህብረተሰብ፣ በትምህርት፣ በግብር እና በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ላይ ትልቅ የህግ ለውጥ አድርጓል።ግዛቱ በባልካን እና በፖላንድ-ሊቱዌኒያ ኮመንዌልዝ ደቡባዊ ክፍል በኩል ወደ መካከለኛው አውሮፓ በሚያደርገው ግስጋሴ ከቅዱስ ሮማ ኢምፓየር ጋር ብዙ ጊዜ ይጋጭ ነበር።የኦቶማን ባህር ኃይል እንደ 1538 ፣ 1571 ፣ 1684 እና 1717 (በዋነኛነት ከሀብስበርግ ስፔን ፣ የጄኖዋ ሪፐብሊክ ፣ የቬኒስ ሪፐብሊክ ፣ የቅዱስ ጆን ፈረሰኞች ፣ ፓፓል ግዛቶች ፣ ግራንድ ያቀፈ) ከመሳሰሉት ከበርካታ ቅዱሳን ሊጎች ጋር ተዋግቷል ። የቱስካኒ ዱቺ እና የሳቮይ ዱቺ)፣ ለሜዲትራኒያን ባህር ቁጥጥር። በምስራቅ፣ ኦቶማኖች በ16ኛው እና በ18ኛው ክፍለ ዘመን መካከል ባለው የግዛት ውዝግብ ወይም በሃይማኖታዊ ልዩነቶች ምክንያት ከሳፋቪድ ፋርስ ጋር ይዋጉ ነበር። የዛንድ፣ የአፍሻሪድ እና የቃጃር ስርወ-መንግስቶች በኢራን ውስጥ የሳፋቪዶችን በመተካት እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ ድረስ የኦቶማን ጦርነቶች ከፋርስ ጋር ቀጥለዋል። በምስራቅ በኩል እንኳን፣ የሀብስበርግ-ኦቶማን ግጭት ማራዘሚያ ነበር፣በዚህም ኦቶማኖች ወታደሮቻቸውን ወደ ሩቅ እና ምስራቃዊ ቫሳል እና ግዛታቸው መላክ ነበረባቸው፣ በደቡብ ምስራቅ እስያ የሚገኘው ሱልጣኔት፣ ከአውሮፓ ቅኝ ገዥዎች እንዲሁም ከ የላቲን ወራሪዎች ከላቲን አሜሪካ ተሻግረው የቀድሞ የሙስሊም የበላይነት የነበረችውን ፊሊፒንስ ክርስትናን ያደረጉ።ከ16ኛው እስከ 20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ድረስ የኦቶማን ኢምፓየር ከሩሲያ ዛርዶም እና ኢምፓየር ጋር አስራ ሁለት ጦርነቶችን ተዋግቷል። እነዚህ በመጀመሪያ ስለ ኦቶማን ግዛት መስፋፋት እና በደቡብ-ምስራቅ እና በምስራቅ አውሮፓ ውስጥ ስለ ማጠናከር ነበር; ነገር ግን ከሩሶ-ቱርክ ጦርነት ጀምሮ በሰሜናዊ ጥቁር ባህር ዳርቻ ላይ ያሉትን ስልታዊ ግዛቶች ወደ ሩሲያውያን እያጣ ስለነበረው የኦቶማን ኢምፓየር ህልውና የበለጠ ሆኑ። ከ 18 ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛ አጋማሽ ጀምሮ የኦቶማን ኢምፓየር ማሽቆልቆል ጀመረ. በ1839 ከመሞቱ በፊት በማሕሙድ የተጀመረው የታንዚማት ተሃድሶ የኦቶማን መንግስት በምዕራብ አውሮፓ ከታየው እድገት ጋር በማጣጣም ዘመናዊ ለማድረግ ያለመ ነው። በታንዚማት መገባደጃ ዘመን ሚድሃት ፓሻ ያደረጉት ጥረት እ.ኤ.አ. የግዛቱ መጠን ቀስ በቀስ እየጠበበ ሲሄድ, ወታደራዊ ኃይል እና ሀብት; በተለይም በ 1875 ከኦቶማን የኢኮኖሚ ቀውስ በኋላ እና በባልካን ግዛቶች ውስጥ ወደ ሩሲያ-ቱርክ ጦርነት ያበቃውን አመፅ አስከትሏል; ብዙ የባልካን ሙስሊሞች የሩስያን የካውካሰስን ወረራ ሸሽተው ከነበሩት ሰርካሲያውያን ጋር አናቶሊያ ወደሚገኘው የኢምፓየር እምብርት ቦታ ተሰደዱ። በሰርካሲያን የዘር ጭፍጨፋ ሩሲያ እስከ 1.5 ሚሊዮን የሚደርሱ ሙስሊም ሰርካሲያውያንን ጨፍጭፋለች፣ የተረፉት በኦቶማን ኢምፓየር ስደተኛ ፈለጉ። የኦቶማን ኢምፓየር ማሽቆልቆል በተለያዩ ርእሰ ብሔር ህዝቦች መካከል የብሔረተኝነት ስሜት እንዲጨምር አድርጓል፣ ይህም የጎሳ ግጭቶች እንዲጨምር አድርጓል፣ ይህም አልፎ አልፎ ወደ ብጥብጥ እንዲፈጠር አድርጓል፣ ለምሳሌ የሃሚዲያን አርመናውያን እልቂትበመጀመርያው የባልካን ጦርነት የሩሜሊያ (በአውሮፓ የኦቶማን ግዛቶች) መጥፋት ተከትሎ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሙስሊም ስደተኞች (ሙሃሲር) ወደ ኢስታንቡል እና አናቶሊያ ደረሱ። ከታሪክ አኳያ፣ የሩሚሊያ ኢያሌት እና አናቶሊያ ኢያሌት የኦቶማን ኢምፓየር አስተዳደራዊ እምብርት መሥርተው ነበር፣ ገዥዎቻቸው ቤይለርቤይ የሚባሉት በሱልጣኑ ዲቫን ውስጥ ይሳተፋሉ፣ ስለዚህ በ1912 በለንደን ኮንፈረንስ መሠረት ከሚድዬ-ኢኔዝ ድንበር ባሻገር ያሉትን የባልካን ግዛቶች ሁሉ ጠፍተዋል። -13 እና የለንደን ውል ለኦቶማን ማህበረሰብ ትልቅ ድንጋጤ ነበር እና የ1913ቱን የኦቶማን መፈንቅለ መንግስት አድርሷል። በሁለተኛው የባልካን ጦርነት ኦቶማኖች በቁስጥንጥንያ ስምምነት መደበኛ የሆነውን የቀድሞ ዋና ከተማቸውን ኤዲርን (አድሪያኖፕል) እና አካባቢዋን በምስራቅ ትራስ ውስጥ ማስመለስ ችለዋል ። እ.ኤ.አ. በ 1913 የተካሄደው መፈንቅለ መንግስት ሀገሪቱን በሦስቱ ፓሻዎች ቁጥጥር ስር በማዋል ሱልጣኖች መህመድ አምስተኛ እና መህመድ 6ኛ ምንም አይነት እውነተኛ የፖለቲካ ሃይል የሌላቸው ተምሳሌታዊ መሪዎች አድርጓቸዋል።የኦቶማን ኢምፓየር ከማዕከላዊ ኃይሎች ጎን በመሆን ወደ አንደኛው የዓለም ጦርነት ገባ እና በመጨረሻ ተሸንፏል። ኦቶማኖች በጋሊፖሊ ዘመቻ የዳርዳኔልስን ባህር በተሳካ ሁኔታ ጠብቀዋል እና በሜሶጶጣሚያ ዘመቻ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ዓመታት ውስጥ በብሪቲሽ ኃይሎች ላይ የመጀመሪያ ድሎችን እንደ ኩት ከበባ ; ነገር ግን የአረቦች አብዮት በመካከለኛው ምስራቅ በኦቶማን ጦር ላይ ማዕበሉን ቀይሮ ነበር። በካውካሰስ ዘመቻ ግን የሩስያ ጦር ኃይሎች ከመጀመሪያው በተለይም ከሳሪቃሚሽ ጦርነት በኋላ የበላይ ነበሩ:: የሩሲያ ጦር ወደ ሰሜናዊ ምስራቅ አናቶሊያ በመዝመት ከአንደኛው የዓለም ጦርነት እስከ ማፈግፈግ ድረስ ከሩሲያ አብዮት በኋላ በብሬስት-ሊቶቭስክ ውል ተቆጣጥሯል። በጦርነቱ ወቅት የግዛቱ አርመናዊ ተገዢዎች በአርሜኒያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ወደ ሶሪያ ተወሰዱ። በዚህ ምክንያት ከ600,000 እስከ 1 ሚሊዮን የሚገመቱ ወይም እስከ 1.5 ሚሊዮን የሚደርሱ አርመኖች ተገድለዋል። የቱርክ መንግስት ድርጊቱን እንደ ዘር ማጥፋት እውቅና ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን አርመኖች ከምስራቃዊው የጦርነት ቀጠና "የተሰደዱ" ብቻ ነው ብሏል። የዘር ማጥፋት ዘመቻዎች እንደ አሦራውያን እና ግሪኮች ባሉ ሌሎች አናሳ ቡድኖች ላይ ተፈፅመዋል። እ.ኤ.አ. ጥቅምት 30 ቀን 1918 የሙድሮስ ጦርን ተከትሎ አሸናፊዎቹ የሕብረት ኃይሎች የኦቶማን መንግሥት በ 1920 በሴቭሬስ ስምምነት በኩል ለመከፋፈል ፈለጉ ። የቱርክ ሪፐብሊክ ከአንደኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የኢስታንቡል እና ኢዝሚር በተባበሩት መንግስታት መያዙ የቱርክ ብሄራዊ ንቅናቄ እንዲቋቋም ምክንያት ሆኗል ። በጋሊፖሊ ጦርነት ወቅት ራሱን የለየው የጦር አዛዥ ሙስጠፋ ከማል ፓሻ መሪነት የቱርክ የነጻነት ጦርነት የተካሄደው የሴቭሬስ ስምምነትን ውሎችን ለመሻር ነበር። እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 18 ቀን 1922 የግሪክ ፣ የአርመን እና የፈረንሣይ ጦር ተባረረ እና በአንካራ የሚገኘው የቱርክ ጊዚያዊ መንግስት በ23 ኤፕሪል 1920 የአገሪቱን ህጋዊ መንግስት ያወጀው ከአሮጌው ህጋዊ ሽግግር መደበኛ ማድረግ ጀመረ። ኦቶማን ወደ አዲሱ የሪፐብሊካን የፖለቲካ ስርዓት. እ.ኤ.አ. ህዳር 1 ቀን 1922 በአንካራ የሚገኘው የቱርክ ፓርላማ የሱልጣኔቱን ስርዓት በመሰረዝ የ623 ዓመታት የንጉሣዊው የኦቶማን አገዛዝ አብቅቷል። እ.ኤ.አ. ሐምሌ 24 ቀን 1923 የላውዛን ስምምነት የሴቭሬስን ውል የተተካው አዲስ የተቋቋመው “የቱርክ ሪፐብሊክ” የኦቶማን ኢምፓየር ተተኪ ግዛት ሉዓላዊነት ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኝ አስችሏል እናም ሪፐብሊኩ በይፋ የታወጀው እ.ኤ.አ. ጥቅምት 1923 በሀገሪቱ አዲስ ዋና ከተማ አንካራ። የላውዛን ኮንቬንሽን በግሪክ እና በቱርክ መካከል የህዝብ ልውውጥ እንዲኖር የሚደነግግ ሲሆን 1.1 ሚሊዮን ግሪኮች ከቱርክ ወደ ግሪክ ለ 380,000 ሙስሊሞች ከግሪክ ወደ ቱርክ እንዲዘዋወሩ አድርጓል ።ሙስጠፋ ከማል የሪፐብሊኩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት ሆኑ እና በመቀጠል ብዙ ማሻሻያዎችን አስተዋውቀዋል። ማሻሻያው ያረጀውን ሃይማኖትን መሰረት ያደረገ እና ብዙ ማህበረሰቦችን የያዘውን የኦቶማን ህገመንግስታዊ ንጉሳዊ አገዛዝ ወደ ቱርክ ሀገርነት ለመቀየር ያለመ ሲሆን በሴኩላር ህገ መንግስት መሰረት እንደ ፓርላማ ሪፐብሊክ የሚተዳደር ነው። እ.ኤ.አ. በ 1934 የአያት ስም ህግ ፣ የቱርክ ፓርላማ ለሙስጠፋ ከማል “አታቱርክ” (አባት ቱርክ) የሚል የክብር ስም ሰጠው። የሞንትሬክስ ኮንቬንሽን የቱርክን የዳርዳኔልስ እና የቦስፖረስ የባህር ዳርቻ የባህር ዳርቻዎችን እና የማርማራ ባህርን ወታደራዊ ለማድረግ እና በጦርነት ጊዜ የባህር ላይ ትራፊክን የመዝጋት መብትን ጨምሮ በቱርክ የባህር ወሽመጥ ላይ የቱርክን ቁጥጥር መልሶ መለሰ። እ.ኤ.አ. በ1923 የቱርክ ሪፐብሊክ ከተመሰረተች በኋላ፣ በኦቶማን ዘመን በመሳፍንት (ጋ) የሚመሩ ፊውዳል (ማኖሪያል) ማህበረሰቦች የነበሩ አንዳንድ የኩርድ እና የዛዛ ጎሳዎች ሀገሪቱን ለማዘመን ባቀዱት የአታቱርክ ተሀድሶዎች ብስጭት ሆኑ። እንደ ሴኩላሪዝም (የሼክ ሰይድ ዓመፅ፣ 1925) እና የመሬት ማሻሻያ (የደርሲም አመጽ፣ 1937–1938)፣ እና በወታደራዊ እንቅስቃሴዎች የተወገዱ የታጠቁ አመጾችን አስነስቷል።ኢስሜት ኢኖኑ በህዳር 10 ቀን 1938 አታቱርክ ከሞቱ በኋላ ሁለተኛው የቱርክ ፕሬዝዳንት ሆነ። እ.ኤ.አ. ሰኔ 29 ቀን 1939 የሃታይ ሪፐብሊክ ቱርክን በህዝበ ውሳኔ እንድትቀላቀል ድምጽ ሰጠ። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ቱርክ ገለልተኛ ሆና ነበር ነገር ግን በየካቲት 23 ቀን 1945 ከአሊያንስ ጎን በመሆን ወደ ጦርነቱ መዝጊያ ደረጃ ገባች ። በሰኔ 26 ቀን 1945 ቱርክ የተባበሩት መንግስታት ቻርተር አባል ሆነች። በሚቀጥለው ዓመት የቱርክ የአንድ ፓርቲ ጊዜ አብቅቶ በ1946 የመጀመሪያው የመድብለ ፓርቲ ምርጫ ተጠናቀቀ። በ1950 ቱርክ የአውሮፓ ምክር ቤት አባል ሆነች።በሴላል ባያር የተቋቋመው ዲሞክራቲክ ፓርቲ እ.ኤ.አ. በ1950፣ 1954 እና 1957 አጠቃላይ ምርጫዎችን አሸንፎ ለአስር አመታት በስልጣን ላይ የቆየ ሲሆን አድናን ሜንዴሬስ ጠቅላይ ሚኒስትር እና ባያር በፕሬዚዳንትነት አገልግለዋል። በኮሪያ ጦርነት የተባበሩት መንግስታት ጦር አካል ሆና ከተዋጋች በኋላ፣ ቱርክ በ1952 ኔቶን ተቀላቀለች፣ የሶቭየት ህብረትን ወደ ሜዲትራኒያን ባህር መስፋፋት ምሽግ ሆናለች። በመቀጠልም ቱርክ በ1961 የኦኢሲዲ መስራች አባል እና በ1963 የኢኢሲዲ ተባባሪ አባል ሆነች። በ1960 እና 1980 በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት፣ እንዲሁም በ1971 እና 1997 በወታደራዊ ማስታወሻዎች፣ በ1960 እና በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ፣ በቱርክ ፖለቲካ ውስጥ ታዋቂ የሆኑ መሪዎች፣ በ1960 እና 1980 ሀገሪቱ የጀመረችውን ግርግር ወደ መድበለ ፓርቲ ዴሞክራሲ ሽግግር ተቋረጠ። የምርጫ ድሎች ሱሌይማን ዴሚሬል፣ ቡለንት ኢሴቪት እና ቱርጉት ኦዛል ናቸው። ለአስር አመታት የቆጵሮስ የእርስ በርስ ግጭት እና በቆጵሮስ ጁላይ 15 ቀን 1974 መፈንቅለ መንግስት በኢኦካ ቢ ፓራሚሊተሪ ድርጅት ፕሬዚደንት ማካሪዮስን አስወግዶ ደጋፊ ኢንኖሲስን (ከግሪክ ጋር ህብረት) ኒኮስ ሳምፕሰንን በአምባገነንነት የመሰረተው ቱርክ በጁላይ 20 ቀን ቆጵሮስን ወረረች። እ.ኤ.አ. በ 1974 በዋስትና ውል ውስጥ አንቀጽ ን በብቸኝነት በመተግበር ፣ ግን በወታደራዊ ሥራው መጨረሻ ላይ ያለውን ሁኔታ ወደነበረበት ሳይመለስ ። እ.ኤ.አ. በ 1983 በቱርክ ብቻ እውቅና ያገኘችው የቱርክ የሰሜን ቆጵሮስ ሪፐብሊክ ተመሠረተች ፣ ደሴቲቱን መልሶ ለማገናኘት የአናን ፕላን በአብዛኛዎቹ የቱርክ የቆጵሮሳውያን ድጋፍ ቢደረግም በብዙዎቹ የግሪክ የቆጵሮስ ሰዎች በ 2004 በተለየ ህዝበ ውሳኔ ውድቅ ተደርጓል ። የቆጵሮስን አለመግባባት ለመፍታት በቱርክ ቆጵሮስ እና በግሪክ የቆጵሮስ የፖለቲካ መሪዎች መካከል ድርድር አሁንም ቀጥሏል። በቱርክ እና በኩርዲስታን የሰራተኞች ፓርቲ (ፒኬኬ) መካከል ያለው ግጭት (በቱርክ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ህብረት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው) ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ በዋነኛነት በደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። በግጭቱ ምክንያት ከ40,000 በላይ ሰዎች ሞተዋል። እ.ኤ.አ. በ1999 የፒኬኬ መስራች አብዱላህ ኦካላን በሽብርተኝነት እና የሀገር ክህደት ክስ ተይዞ ተፈርዶበታል። ከዚህ ባለፈም የተለያዩ የኩርድ ቡድኖች ከቱርክ ለመገንጠል ነፃ የኩርድ መንግስት ለመፍጠር ሲፈልጉ ሌሎች ደግሞ በቅርብ ጊዜ የክልል ራስን በራስ የማስተዳደር እና በቱርክ ውስጥ ለኩርዶች ፖለቲካዊ እና ባህላዊ መብቶችን ተከትለዋል ። በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን በቱርክ ውስጥ አናሳ ብሄረሰቦችን ባህላዊ መብቶች ለማሻሻል አንዳንድ ማሻሻያዎች ተካሂደዋል, ለምሳሌ እና አቫዝ በ .እ.ኤ.አ. በ 1980 ዎቹ የቱርክ ኢኮኖሚ ነፃ ከወጣች በኋላ ሀገሪቱ ጠንካራ የኢኮኖሚ እድገት እና የላቀ የፖለቲካ መረጋጋት አግኝታለች። ቱርክ እ.ኤ.አ. የሰብአዊ መብት ጥሰትን እና የህግ የበላይነትን በመጥቀስ ከቱርክ ጋር የአውሮፓ ህብረት አባልነት ውይይት; ከ2018 ጀምሮ በውጤታማነት የቆመ ድርድሩ፣ እስከ 2020 ድረስ ንቁ ሆኖ ይቆያል። እ.ኤ.አ. በ 2013 በብዙ የቱርክ ግዛቶች ሰፊ ተቃውሞ ተቀስቅሷል ፣ይህም የጌዚ ፓርክን ለማፍረስ በወጣው እቅድ የተቀሰቀሰ ቢሆንም ብዙም ሳይቆይ ወደ አጠቃላይ ፀረ-መንግስት ተቃውሞ ማደጉ። እ.ኤ.አ. ጁላይ 15 ቀን 2016 ያልተሳካ መፈንቅለ መንግስት መንግስትን ከስልጣን ለማውረድ ሞክሯል። ለከሸፈው መፈንቅለ መንግስት ምላሽ መንግስት የጅምላ ማፅዳትን አድርጓል። በጥቅምት 9 እና 25 ህዳር 2019 መካከል ቱርክ በሰሜን ምስራቅ ሶሪያ ወታደራዊ ጥቃት አድርጋለች። በኅዳር 20 ቀን 2009 ዓም፣ የቱርክ ፕሬዚዳንት ረጀፕ ታይፕ እርዶዋን እንዲህ ብሏል፦ «ሥራዊታችን ወደ ሶርያ የገቡበት ምክንያት፣ የባሻር አል-አሣድን መንግሥት ለማስጨርስ ነው።» ስለዚህ፣ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት፣ ከቱርክ መንግሥትና ከሶርያ መንግሥት መካከል አሁን በይፋ የጦርነት ሁኔታ አለ። በሚያዝያ 21 ቀን እርዶዋን ባለ-ሙሉ-ሥልጣን ደረጃ በይፋ ወሰደ፤ በቱርክ አገር ደግሞ ውክፔድያ ድረ ገጽ በማናቸውም ቋንቋ ታግድል። ውክፔድያ በቱርክ የተገደበበት ምክንያት የቱርክ መንግሥት ለሽብርተኞች እርዳታ እንደሚሰጥ የሚል ማስረጃ ስላቀረበ ነው። ታዋቂ ሰዎች ሙስታፋ ኬማል አታቱርክ
9876
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%A5%E1%89%B5%20%E1%8B%98%E1%8B%8D%E1%8B%B2%E1%89%B1
ንግሥት ዘውዲቱ
ግርማዊት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ቅዳሜ ሚያዝያ ፳፪ ቀን ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ከሸዋ ንጉሥ ምኒልክና ከወረኢሉ ተወላጅ ከወይዘሮ አብቺው በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ በሞረትና ጅሩ ወረዳ እነዋሪ ከተማ አጠገብ በምትገኝ ሰገነት በምትባል መንደር ተወለዱ። ሐምሌ ፲፩ ቀን ሰኞ ሥርዓተ ጥምቀት ተፈጽሞላቸው፣ የክርስትና ስማቸው አስካለ ማርያም ተባለ። ግርማዊት ንግሥተ ነገሥት ዘውዲቱ ለዳግማዊ ምኒልክ ሦስተኛ ልጅ ሲሆኑ ከልጅ ኢያሱ ቀጥለው መኳንንትና ሕዝቡ መክሮና ዘክሮ በምርጫ በኢትዮጵያ ዙፋን ላይ የተቀመጡ ብቸኛዋ ንግሥት ናቸው። አባታቸው የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ (በኋላ ዳግማዊ ዐፄ) ዘውዲቱ የስድስት ዓመት ሕጻን እንደነበሩ ለአሥራ ሁለት ዓመቱ የዐፄ ዮሐንስ ልጅ ለአርአያ ሥላሴ ዳሩዋቸው። ጋብቻቸውም ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ.ም. በተክሊልና በቁርባን ተፈጸመ፡ የሠርጉም ማማርና የሽልማቱ ብዛት ሊነገር አይቻልም። ልጅ ኢያሱ መስከረም ፲፯ ቀን ፲፱፻፱ ዓ.ም ከስልጣን ሲወርዱ፤ መኳንንቱና ሕዝቡ መክሮና ዘክሮ በምርጫ ወይዘሮ ዘውዲቱን ግርማዊት ንግሥተ ነገሥት፤ ራስ ተፈሪ መኮንንን አልጋ ወራሽ እና ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴ እንዲሆኑ ወስነው መስከረም ፳፩ ቀን "ግርማዊት ዘውዲቱ፣ ንግሥተ ነገሥት ዘኢትዮጵያ" ተብለው ነገሡ። በመኳንንቱም ምክር መሠረት ጳጳሱና እጨጌ ወልደጊዮርጊስ "ኢያሱን የተከተልክ፣ ያነገሥናትን ዘውዲቱንና ራስ ተፈሪን የከዳህ፣ ውግዝ ከመአርዮስ" እያሉ በአዋጅ አወገዙ፡ ከዚህ በኋላ በጥቅምት የሰገሌ ጦርነት ከተደረገ በኋላ የዘውድ በዓሉ የካቲት ፬ ቀን ፲፱፻፱ ዓ.ም እንዲሆን ታዞ፣ ለዘውዱ በዓል በኢትዮጵያ አዋሳኝ ያሉት የእንግሊዝ ሱዳንና የእንግሊዝ ሱማሌ ገዥዎች፤ የፈረንሳይ ሱማሌ ገዥ እና በኢትዮጵያም ታላላቅ ራሶች እንዲሁም የየአውራጃው ገዥዎች በተገኙበት በዕለተ እሑድ አባታቸው ባሠሩት በትልቁ ደብር በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በሊቀ ጳጳሱ በአቡነ ማቴዎስ እጅ ቅብዐ መንግስት ተቀብተው የንጉሠ ነገሥቱን ዘውድ ጫኑ። ከዚህም በኋላ እንደ ሥርዓተ ንግሡ ሕግ፤ ንግሥተ ነገሥት ዘውዲቱ በአባታቸው ዙፋን ተቀምጠው መንገሣቸውን፤ ደጃዝማች ተፈሪም ራስ ተብለው አልጋ ወራሽና ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴ መሆናቸውን በቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በተሰበሰበው ሕዝብ ፊት አዋጅ ተነገረ። የንግሥተ ነገሥታትን ሥልጣን ለማሳወቅ ሲባል ራስ ወልደ ጊዮርጊስ የካቲት ፲፩ ቀን ራስ ወልደ ጊዮርጊስን ንጉሠ ጎንደር ብለው አንግሠው ዘውድ ደፉላቸው። እንደዚሁም መስከረም ፳፯ ቀን 1921 ዓ.ም. ብዙ መኳንንትና መሣፍንት፤ ሊቃውንትና ጳጳሳት ባሉበት የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ መኮንንን አዲስ አበባ መካነ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን፣ ንጉሥ ተፈሪ ተብለው ዘውድ ተጫነላቸው። ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ በነገሡ በአሥራ ሦሥት ዓመት ተኩል በ፶፬ ዓመት ዕድሜያቸው ረቡዕ መጋቢት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፪ ዓ.ም በ ፰ ሰዓት ዐረፉ። የሞታቸው ዜና እንደተሰማም በከተማው የሐዘን ጥላ አጠላበት። አባታቸው ዐፄ ምኒልክ በተቀበሩበት በታዕካ ነገሥት በዓታ ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። በግርማዊት ንግሥተ ነገሥት ዘውዲቱ ዘመን ከተፈጸሙ ተግባራት የዓለም ማኅበር አባልነት የዓለም መንግሥታት ማኅበር (ሊግ ኦፍ ኔሽንስ) ጠቅላላው ጉባዔ በ28 ሴፕቴምበር በ1923 እ.ኤ.አ. (መስከረም 17 1916 ዓ.ም.) ስብሰባውን ቀጠሉና የስድስተኛውን ኮሚሲዮን ማስታወቂያ ተደግፎ ኢትዮጵያ ማኅበርተኛ እንድትሆን ፈቃዱ መሆኑን አስታወቀ። በዚህ ጊዜ ዋናው መልእክተኛ ደጃዝማች ናደው የደስታ ስሜታቸውን ለመግለጥ ንግግር ማድረጊያው ስፍራ ላይ ቆመው የሚከተለውን ዲስኩር ተናገሩ፡፡ ክቡራን ሆይ፤ ጠቅላላው ጉባኤ በበጎ ፈቃደኝነትና በትክክለኛ ፈራጅነት፣ በጥልቅ አስተሳሰብ መርምሮ ወደ ማኅበሩ ስለመግባት ያቀረብነውን ጥያቄ ስለ ተቀበለው፣ የኢትዮጵያ መልእክተኞች በግርማዊት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱና በልዑል ራስ ተፈሪ መኰንን የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽና ባለ ሙሉ ሥልጣን እንደራሴ ስም፣ እንዲሁም በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ምስጋና ያቀርባሉ። የሰውን ልጅ ወንድማማችነት የመመሥረት ዓላማ ባለው ውሳኔያችሁ የተሰማንንም ልባዊ ደስታ እንድገልጽላችሁ ይፈቀድልኝ ዘንድ እለምናለሁ። ኢትዮጵያ ባለፈው የጀግንነት ታሪክና በከፍተኛ ሥልጣኔዋ የምትኮራ አገር መሆንዋ፣ የዘመናዊ ድርጅቶች ከሚያስገኙላትም ፍሬ ተካፋይ ለመሆን ብርቱ ጥረትና ሙሉ ፈቃደኛነት እንዳላት የታወቀ ነው። መንግሥታችንም ይህን ጥረት ወደ መልካም ግብ ለማድረስ የዓለም መንግሥታትን አንድነትና ኅብረት የሚያስፈልግ መሆኑን በጥብቅ ያምንበታል። ስለ ባሮች የነፃነት ደንብ ልዑል አልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ መጋቢት ፲፮ ቀን ፲፱፻፲፮ ዓ.ም በግርማዊት ንግሥት ዘውዲቱ ፈቃድ ስለ ባሮች ነፃነት አንድ ደንብ አወጡ። ደንቡ «ስለ ባሮች አስተዳደርና ነፃነት የቆመ ደንብ» የሚል አርእስት ተሰጥቶትና እንደ መጽሐፍ ሆኖ በልዑል አልጋ ወራሽ ማተሚያ ቤት ታትሞ ወጣ። መጽሐፉ ባለ 10 ገጽ ሲሆን የደንቡ ቃል በ45 ቁጥሮች ተመድቧል፡፡ ይህ መጽሐፍ ለሕዝብ ይሸጥ ነበርና መጽሐፉን ገዝቶ ያነበበው አብዛኛው ሰው «የሥልጣኔ እርምጃ ነው» እያለ አልጋ ወራሽን አመሰገነ። ባለብዙ ባሮች የሆኑት ሰዎች ግን በልባቸው ቅሬታ ገብቶ አዘኑ። ለምሳሌ የጦር ሚኒስትሩ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ በዚያው ሰሞን የልባቸውን ቅርታ በጨዋታ ላይ ሲናገሩ «እንግዲህ ምን አለ አልታየ ወርቅ (ሚስታቸው) ወደ ወንዝ እየወረደች ውሀ መቅዳት ነው፣ እኔም እንጨት እየፈለጥሁ አቀርብላታለሁ» አሉ እየተባለ ሲወራላቸው ከረመ፡፡ የአፄ ቴዎድሮስ ዘውድ ስለ መመለሱ ከእንግሊዝ አገር የመጣው የአፄ ቴዎድሮስ ዘውድ ሐምሌ 4 ቀን 1917 ዓ.ም ቅዳሜ ለግርማዊት ንግሥት ዘውዲቱ ተመለሰ። በዚህም ጊዜ የተፈጸመው ሥነ ሥርዓት እንደሚከተለው ነበር፤ ከጧቱ በ4 ሰዓት የግቢ ሚኒስትር ደጃዝማች ወልደ ገብርኤል በሻህ በጦር ልብስ ያጌጡ ጭፍሮች አስከትለውና በአራት ፈረሶች የሚሳብ ሠረገላ አሲዘው ከአቶ ሣህሌ ፀዳሉ ጋር ወደ እንግሊዝ ሌጋሲዮን ሄዱ። የእንግሊዝ መንግሥት ሚኒስትር ሚስተር ቻርልስ ቤንቲንክም ዘውዱን በሠረገላው ላይ አስቀመጡትና ሁሉም ዘውዱን አጅበው ወደ ቤተ መንግሥት መጡ። ግርማዊት ንግሥት ዘውዲቱና ልዑል አልጋ ወራሽ በቤተ መንግሥታቸው ውስጥ በተለይ በተሰናዳው ስፍራ ከመኳንንት ጋር ተቀምጠው ይጠብቁ ነበር። የግቢ ዘበኞችም በግቢው ውስጥ በቀኝና በግራ ተሰልፈው ነበርና ሠረገላው በሰልፉ መካከል አልፎ ከመንግሥት ፊት ደረሰ። እዚያም አንድ ጠረጴዛ ተዘጋጅቶ ነበርና ሚስተር ቤንቲንክ ዘውዱን ከሠረገላው አውርደው በጠረጴዛው ላይ አስቀመጡትና ከዚህ ቀጥሎ ያለውን ቃል ተናገሩ፤ ግርማዊት ሆይ በንግሥት ቪክቶሪያ መንግሥት በ1860 ዓ.ም ከመቅደላ የተወሰደውን የአፄ ቴዎድሮስን ዘውድ የታላቂቱ ብሪታንያና የአየርላንድ፣ ከባሕር ማዶ ያሉት ግዛቶች ንጉሥና የህንድ ንጉሠ ነገሥት በሆኑት በግርማዊ ጌታዬ በንጉሡ ትዕዛዝ ለግርማዊት ንግሥት በማክበር እመለስሁ። (መርስዔ ኀዘን ወ/ቂርቆስ፣ የሐያኛ ክፍለ ዘመን መባቻ፣ 2000) ዋቢ መጻሕፍት እና ማስታወሻ ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ -ቀ.ኃ.ሥ 1929 ዓ.ም - ገጽ 37-38 አጤ ምኒልክ - ከጳውሎስ ኞኞ1984 ዓ.ም -ገጽ 77 ''የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል በ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ 1999 ዓ.ም. ገጽ 136
49264
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AA%E1%88%9D%20%E1%8C%86%E1%8A%95%E1%8C%8D%20%E1%8A%A1%E1%8A%95
ኪም ጆንግ ኡን
ኪም ጆንግ-ኡን[/; ኮሪያኛ: , ኮሪያኛ: []፤ ጥር 8 ቀን 1983 ተወለደ) የሰሜን ኮሪያ ከፍተኛ መሪ የነበረ የሰሜን ኮሪያ ፖለቲከኛ ነው። ኮሪያ ከ 2011 ጀምሮ እና ከ 2012 ጀምሮ የኮሪያ የሰራተኞች ፓርቲ () መሪ. ከ 1994 እስከ 2011 ሁለተኛው የሰሜን ኮሪያ ከፍተኛ መሪ የነበረው የኪም ጆንግ-ኢል ልጅ እና ኮ ዮንግ-ሁይ ናቸው. እ.ኤ.አ. በ1948 የሰሜን ኮሪያ መስራች እና የመጀመሪያ የበላይ መሪ የነበሩት የኪም ኢል ሱንግ የልጅ ልጅ ናቸው። እ.ኤ.አ. ከ2010 መጨረሻ ጀምሮ ኪም የሰሜን ኮሪያን አመራር ተተኪ ተደርጎ ይታይ ነበር። በታህሳስ 2011 የአባቱን ሞት ተከትሎ የመንግስት ቴሌቪዥን ኪምን "ታላቅ ተተኪ" ብሎ አስታወቀ። ኪም የኮሪያ የሰራተኞች ፓርቲ ዋና ፀሀፊ፣ የማዕከላዊ ወታደራዊ ኮሚሽን ሊቀ መንበር እና የመንግስት ጉዳዮች ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ማዕረግን ይዟል። እንዲሁም ከፍተኛው ውሳኔ ሰጪ አካል የሆነው የኮሪያ የሰራተኞች ፓርቲ ፖሊት ቢሮ ፕሬዚዲየም አባል ነው። እ.ኤ.አ. በጁላይ 2012 ኪም የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ በመሆን ስልጣኑን በማጠናከር በኮሪያ ህዝብ ጦር ውስጥ የማርሻል ከፍተኛ ማዕረግ አግኝቷል። የሰሜን ኮሪያ የመንግስት ሚዲያዎች ብዙ ጊዜ "ማርሻል" ወይም "ውድ የተከበሩ መሪ" ብለው ይጠሩታል። እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ ከኪም ኢል ሱንግ ፖሊሲ ጋር የሚመሳሰል የቢንግጂን ፖሊሲን አስተዋውቋል ፣ ይህም የሁለቱም ኢኮኖሚ እና የሀገሪቱን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልማት በአንድ ጊዜ በማጣቀስ ነው። ኪም ሰሜን ኮሪያን እንደ ፍፁም አምባገነንነት የሚገዙ ሲሆን አመራሩም እንደ አያቱ እና አባቱ ተመሳሳይ የስብዕና አምልኮን ተከትሏል። እ.ኤ.አ. በ 2014 የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ዘገባ ኪም በሰብአዊነት ላይ በፈጸሙ ወንጀሎች ክስ ሊመሰረት እንደሚችል ጠቁሟል ። በርካታ የሰሜን ኮሪያ ባለስልጣናት እንዲፀዱ ወይም እንዲገደሉ አዟል። እ.ኤ.አ. በ2017 የግማሽ ወንድሙ ኪም ጆንግ-ናም በማሌዥያ እንዲገደል እንዳዘዘ በብዙዎች ዘንድ ይታመናል። የፍጆታ ኢኮኖሚ መስፋፋትን፣ የግንባታ ፕሮጀክቶችን እና የቱሪስት መስህቦችን መርተዋል። ኪም የሰሜን ኮሪያን የኒውክሌር መርሃ ግብር በማስፋት ከዩናይትድ ስቴትስ እና ከደቡብ ኮሪያ ጋር ከፍተኛ ውጥረት እንዲፈጠር አድርጓል። እ.ኤ.አ. በ2018 እና 2019 ኪም ከደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ሙን ጄ ኢን እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በመሪዎች ላይ ተሳትፈዋል። በሰሜን ኮሪያ የ -19 ወረርሽኝን በመዋጋት ረገድ ስኬታማ መሆኑን ተናግሯል ፣ ምንም እንኳን ብዙ ባለሙያዎች አገሪቱ በአጠቃላይ ምንም ዓይነት ጉዳዮች እንደሌሏት ቢጠራጠሩም የመጀመሪያ ህይወት የሰሜን ኮሪያ ባለስልጣናት እና የመንግስት መገናኛ ብዙሃን የኪም የልደት ቀን 8 ጃንዋሪ 1982 ነበር, ነገር ግን የደቡብ ኮሪያ የስለላ ባለስልጣናት ትክክለኛው ቀን ከአንድ አመት በኋላ እንደሆነ ያምናሉ.የኪም ይፋዊ የልደት አመት በምሳሌያዊ ምክንያቶች ተለውጧል ተብሎ ይታሰባል; እ.ኤ.አ. በ1982 አያቱ ኪም ኢል ሱንግ ከወለዱ 70 ዓመታት በኋላ እና አባቱ ኪም ጆንግ-ኢል በይፋ ከወለዱ 40 ዓመታት በኋላ ነው። ከ2018 በፊት የዩኤስ የግምጃ ቤት ዲፓርትመንት የኪም ጆንግ ኡን ይፋዊ የልደት ቀን እ.ኤ.አ. ጥር 8 ቀን 1984 ሲል ዘርዝሯል። እ.ኤ.አ. በ1984 ተወለደ የሚለው አባባል በ1998 ወደ አሜሪካ በሄዱት አክስቱ እና አጎቱ በሲአይኤ ከጠየቁት ግጥሚያዎች ጋር። ኪም ጆንግ-ኡን ለኪም ጆንግ-ኢል ከወለዱት ሶስት ልጆች መካከል ሁለተኛዋ ኮ ዮንግ-ሁዊ ነው; ታላቅ ወንድሙ ኪም ጆንግ ቹል እ.ኤ.አ. በ 1981 ተወለደ ፣ ታናሽ እህቱ ኪም ዮ-ጆንግ በ1987 እንደተወለደች ይታመናል ። እሱ የሰሜን ኮሪያ መስራች እና መሪ የነበረው የኪም ኢል ሱንግ የልጅ ልጅ ነው። ከተመሠረተበት 1948 ጀምሮ እስከ ዕለተ ሞቱ 1994 ዓ.ም. ሁሉም የኪም ጆንግ-ኢል ልጆች በስዊዘርላንድ ውስጥ እንደነበሩ ይነገራል, እንዲሁም የሁለቱ ታናናሽ ወንድ ልጆች እናት, በጄኔቫ ለተወሰነ ጊዜ የኖሩት. የመጀመሪያዎቹ ዘገባዎች ኪም ጆንግ ኡን ከ1993 እስከ 1998 በስዊዘርላንድ ጓምሊገን በሚገኘው የበርን የግል ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት ‹› ወይም “” በሚል ስያሜ የተማረ መሆኑን ገልፀው ከ1993 እስከ 1998 ዓ.ም. ዓይናፋር፣ ጥሩ ጥሩ ተማሪ እንደነበር ተነግሯል። ከክፍል ጓደኞቹ ጋር በጥሩ ሁኔታ, እና የቅርጫት ኳስ ደጋፊ ነበር. የእሱ ጠባቂ ነው ተብሎ በሚገመተው አንድ ትልቅ ተማሪ ገፋፍቶታል። ነገር ግን በኋላ ላይ የጉምሊገን ትምህርት ቤት ተማሪ ኪም ጆንግ-ኡን ሳይሆን ታላቅ ወንድሙ ኪም ጆንግ-ቹል እንደሆነ ተጠቁሟል።በኋላ፣ ኪም ጆንግ-ኡን ከ1998 እስከ 2000 ድረስ የሰሜን ኮሪያ ኤምባሲ ሰራተኛ ልጅ ሆኖ በበርን አቅራቢያ በሚገኘው ኮኒዝ በሚገኘው የሊበፌልድ ስታይንሆልዝሊ ግዛት ትምህርት ቤት “ፓክ-ኡን” ወይም “ኡን-ፓክ” በሚል ስያሜ እንደተማረ ተዘግቧል። በርን. የሰሜን ኮሪያ ተማሪ በዚያ ወቅት ትምህርት ቤቱን መማሩን ባለስልጣናት አረጋግጠዋል። ፓክ-ኡን በመጀመሪያ የውጪ ቋንቋ ለሚማሩ ህጻናት ልዩ ክፍል የተማረ ሲሆን በኋላም በመደበኛው የ6ኛ፣ 7ኛ፣ 8ኛ እና የመጨረሻው 9ኛ አመት ክፍል ተካፍሏል በ2000 መገባደጃ ላይ በድንገት ትምህርት ቤቱን ለቅቋል። የቅርጫት ኳስ መጫወት የሚወድ - የተዋሃደ እና ከፍተኛ ፍላጎት ያለው ተማሪ። ነገር ግን ውጤቱ እና የመገኘት ደረጃው ደካማ እንደነበር ተዘግቧል። በስዊዘርላንድ የሰሜን ኮሪያ አምባሳደር ሪ ቾል ከእሱ ጋር የቅርብ ግንኙነት ነበራቸው እና እንደ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል። ከፓክ-ዩን አብረው ከሚማሩት አንዱ የሰሜን ኮሪያ መሪ ልጅ እንደሆነ እንደነገረው ለጋዜጠኞች ተናግሯል። አንዳንድ ዘገባዎች እንደሚያሳዩት ኪም በክፍል ጓደኞቻቸው ዘንድ ከልጃገረዶች ጋር የማይመች እና ለፖለቲካዊ ጉዳዮች ደንታ ቢስ የሆነ አይናፋር ልጅ ነበር፣ ነገር ግን በስፖርቱ ራሱን የለየ እና በአሜሪካ ብሄራዊ የቅርጫት ኳስ ማህበር እና በሚካኤል ዮርዳኖስ ዘንድ ፍቅር ነበረው። አንድ ጓደኛው ከኮቤ ብራያንት እና ከቶኒ ኩኮቾ ጋር የፓክ-ኡን ፎቶ እንደታየው ተናግሯል። እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 2012 ኪም ጆንግ-ኡን ከ1991 ወይም 1992 ጀምሮ በስዊዘርላንድ እንደኖሩ የሚጠቁሙ አዳዲስ ሰነዶች ወጡ። በፈረንሣይ ሊዮን ዩኒቨርሲቲ የአናቶሚክ አንትሮፖሎጂ ላብራቶሪ በ1999 በሊበፌልድ ስታይንሆልዝሊ ትምህርት ቤት የተወሰደውን የፓክ-ዩን ሥዕል ከኪም ጆንግ-ኡን ሥዕል ጋር እ.ኤ.አ. እነሱ ተመሳሳይ ሰው እንደሆኑ በመጥቀስ። ዋሽንግተን ፖስት እ.ኤ.አ. በ2009 እንደዘገበው የኪም ጆንግ ኡን የትምህርት ቤት ጓደኞች “የቺካጎ ቡልስ ዋና ኮከብ ሚካኤል ዮርዳኖስን ከፍተኛ የእርሳስ ስዕሎችን በመስራት ብዙ ሰዓታትን እንዳጠፋ” አስታውሰዋል። እሱ በቅርጫት ኳስ እና የኮምፒውተር ጨዋታዎች ተጠምዶ ነበር፣ እና የጃኪ ቻን አክሽን ፊልሞች አድናቂ ነበር። ከ2002 እስከ 2007 ኪም ጆንግ ኡን በኪም ኢል ሱንግ ዩኒቨርሲቲ በፒዮንግያንግ መሪ የመኮንኖች ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ገብቷል ። ኪም ሁለት ዲግሪዎችን እንዳገኘ ፣ አንደኛው በኪም ኢል ሱንግ ዩኒቨርሲቲ በፊዚክስ እና ሌላኛው በወታደራዊ መኮንንነት እንደተቀበለ ብዙ ተንታኞች ይስማማሉ። ኪም ኢል ሱንግ ወታደራዊ ዩኒቨርሲቲ ። እ.ኤ.አ. በየካቲት 2018 መገባደጃ ላይ ሮይተርስ እንደዘገበው ኪም እና አባቱ በተለያዩ ሀገራት ቪዛ ለማግኘት በብራዚል የተሰጡ እና በየካቲት 26 ቀን 1996 የተጭበረበሩ ፓስፖርቶችን ተጠቅመዋል። ሁለቱም የ10 አመት ፓስፖርቶች "የብራዚል ኢምባሲ በፕራግ" የሚል ማህተም አላቸው። የኪም ጆንግ ኡን ፓስፖርት "ጆሴፍ ፕዋግ" የሚለውን ስም እና የተወለደበትን ቀን የካቲት 1 1983 መዝግቧል። ለብዙ አመታት የተረጋገጠ አንድ ፎቶ ብቻ ከሰሜን ኮሪያ ውጭ እንዳለ ይታወቃል፣ በ1990ዎቹ አጋማሽ ላይ የተነሳው ይመስላል፣ እሱ አስራ አንድ ነበር። አልፎ አልፎ፣ ሌሎች የእሱ ምስሎች ይታዩ ነበር ነገር ግን ብዙ ጊዜ አከራካሪ ነበሩ። እ.ኤ.አ. በሰኔ 2010 ነበር ፣ እሱ ኦፊሴላዊ ልጥፎችን ከመሰጠቱ እና ለሰሜን ኮሪያ ህዝብ በይፋ ከማወቁ በፊት ፣ ኪም በስዊዘርላንድ ትምህርት ቤት ሲማር የተነሱት ተጨማሪ ምስሎች የተለቀቁት። በጉልምስና የታየበት የመጀመሪያው ይፋዊ ምስል እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 30 ቀን 2010 የተለቀቀው የቡድን ፎቶግራፍ ነበር ፣ እሱን በብቃት የቀባው የፓርቲው ጉባኤ መጨረሻ ላይ ፣ ከፊት ለፊት በተቀመጠው ፣ ከአባቱ ሁለት ቦታዎች ። ይህን ተከትሎ በኮንፈረንሱ ላይ ሲገኝ የሚያሳይ የዜና ዘገባ ቀርቧል።
1547
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8B%B2%E1%88%B5%20%E1%8A%A0%E1%89%A0%E1%89%A3
አዲስ አበባ
አዲስ አበባ () ወይም በረራ ፣አዱ ገነት ወይም በተለምዶ "ሸገር" የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት ። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገመንግስት የፌደራል ከተማነትን ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በ1999 አ.ም በተደረገው የህዝብ ቆጠራ ወደ 2,739,551 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ ትልቋ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍልውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን ወደ አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ነች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። ቅድመ ታሪክ በዓለም ዙሪያ ካሉ ወደ 1,000 የሚጠጉ ሰዎች በዘረመል መረጃ ላይ የተመሰረተ ጥናት የሰው ዘር ከአዲስ አበባ ቅርብ ከሆነ ቦታ ከ100,000 ዓመታት በፊት እንደተበተነ ያመለክታል። መካከለኛው ዘመን የመካከለኛው ዘመን ነገሥታት መዲና የነበረው በራራ ተብሎ ለሚጠራው ቦታ ከቀረቡት ጥቂት ቦታዎች መካከል ከአሁኑ አዲስ አበባ በስተሰሜን የሚገኘው እንጦጦ ተራራ ላይ ያለ ከፍ ያለ ጠፍጣፋ መሬት ነው። ይህ ቦታ እስከ 16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የዐጼ ልብነ ድንግል አገዛዝ ድረስ የበርካታ ነገስታት ዋና መኖሪያ ሆኖ አገልግሏል። በ1442 ዓ.ም አካባቢ ጣሊያናዊው የካርታ ባለሙያ ፍራ ማውሮ ባሳለው ካርታ ላይ ከተማዋን በዝቋላ ተራራ እና በመንጋሻ መካከል አስቀምጧታል። ሆኖም ግን የመናዊው ጸሃፊ አረብ-ፋቂህ እንደዘገበው በ1521 ዓ.ም የንጉሠ ነገሥቱ ጦር ከአዋሽ ወንዝ በስተደቡብ ተይዞ ሳለ በግራኝ አህመድ ተመትታለች። በራራ የሚገኘው በእንጦጦ ተራራ ላይ ነው የሚለው ሀሳብ የሚደግፈው በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ የተመሰረተውና በዓለት በተፈለፈለው ዋሻ ሚካኤል እና በእንጦጦ ማርያም ቤተ ክርስቲያን መካከል የሚገኝ ትልቅ የመካከለኛው ዘመን ከተማ በመገኘቱ ነው። በ30 ሄክታር ቦታ ለ ያረፈው ይህ ጥንታዊ ከተማ ከ 520 ሜትር የድንጋይ ግንብ እስከ 5 ሜትር ቁመት ያላቸው 12 ማማዎች ያሉት ቤተመንግስት ያካትታል። ከከተማዋ በፊት የኢትዮጵያ ዋና ከተማ የነበረችው እንጦጦ የተመሰረተችው በዳግማዊ ዐጼ ምኒልክ በ1871 ዓ.ም ነበር። በወቅቱ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ንጉስ የነበሩት ምኒልክ የእንጦጦ ተራራን በደቡብ ወታደራዊ ዘመቻቸው ጠቃሚ መሰረት አድርገው አገኙት። በስፍራው የነበረውንም ፍርስራሽ እና ያልተጠናቀቀ የመካከለኛው ዘመን ውቅር ቤተክርስቲያን ጎበኙ። ሚስታቸው እቴጌ ጣይቱ ቤተክርስቲያን በእንጦጦ ላይ መስራት በጀመሩበት ወቅት፣ የምኒሊክ ዝንባሌ ወደእዚህ ስፍራ በተለይ ተሳበ፤ ሁለተኛም ቤተክርስቲያን ባቅራቢያው ሠሩ። ነገር ግን ማገዶም ሆነ ውኃ በማጣት ምክንያት አካባቢው መንደር ለመመሥረት አይመችም ነበር፤ ስለዚህ ሰፈራው የጀመረበት ከተራራው ትንሽ ወደ ደቡብ በሚገኘው ሸለቆ ውስጥ በ1878 ነበረ። እቴጌ ጣይቱ እርሳቸውና የሸዋ ቤተመንግስት ወገን መታጠብ ይወዱ የነበረበት ፍልወሃ ምንጭ አጠገብ ለራሳቸው ቤት ሠሩ። አዲስ አበባ (ወይም ባጭሩ «አዲስ») ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ ዓ.ም. ፍልወሃ ምንጭ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። ከእዚያ በኋላ ሌሎች መኳንንቶች ከነቤተሰቦቻቸው አቅራቢያውን ሠፈሩ፤ ምኒልክም የሚስታቸውን ቤት ቤተመንግሥት እንዲሆን አስፋፉትና እስከ ዛሬ ድረስ ቤተ መንግሥት ሆኖ ቆይቷል። ምኒልክ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት በሆነበት ወቅት በ1881 ዓ.ም አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ሆነች። ከእዚያ ጀምሮ ከተማዋ ለመኳንንቶች ብቻ ሳይሆን የእጅ ጥበብ ባለሙያዎችን፣ ነጋዴዎችን እና የውጭ ሀገር ጎብኝዎችን ጨምሮ በርካታ የስራ ክፍሎችን በመሳብ አደገች። ቀደምት የመኖሪያ ቤቶች ጎጆዎች ነበሩ። የአዲስ አበባ ዕድገት የጀመረው ያለቅድመ ዕቅድ በተከሰተ ፈጣን የከተማ መስፋፋት ነው። ከአፄ ምኒልክ አስተዋፅዖዎች አንዱ ዛሬም በከተማው ጎዳናዎች የሚታዩት በርካታ የባሕር ዛፎች ተከላ ነው። እንደ ሪቻርድ ፓንክረስት ገለጻ የከተማዋ የተፋጠነ የህዝብ ቁጥር መጨመር ምክንያት በጊዜያዊ ገዥዎች እና በወታደሮቻቸው፣ በ1892 ረሃብ እና የአድዋ ጦርነት ምክንያት ነው። ሌላው የ1899 የመሬት ህግ፣ በ1901 የማዘጋጃ ቤት አስተዳደር እና ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበረው የባቡር እና የዘመናዊ የትራንስፖርት ስርዓት እድገት ነው። 20ኛው ክፍለ ዘመን ቅድመ-ጣሊያን ወረራ በ1908 አቶ ገብረህይወት ባይከዳኝ የዋና ዋና የአስተዳደር ክፍሎችና የኢትዮ– ጅቡቲ የባቡር መስመር አስተዳዳሪ ሆኑ። በ1909 ራስ ተፈሪ መኮንን፣ (በኋላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ) ከተሾሙ በኋላ በከተማዋ ከፍተኛ ሰው ነበሩ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ራስ ተፈሪ በ1910 እንደ እንደራሴ ህጋዊ ስልጣን አግኝተዋል። የዘመናዊነትንና ከተሜነትን አስፈላጊነት በመገንዘብም ከተማዋን ወደ ለውጥ ለማምጣት ጥረት ያበረከቱ ሲሆን ሀብት ክፍፍልም አድርገዋል። በ1918 እና 1919 መጠነ ሰፊ የኢኮኖሚ አብዮት ተፈጠረ ፣ በካፒታል ክምችት ምክንያት የተትረፈረፈ የቡና ምርት ማደግ ጀመረ ።መካከለኛው የህብረተሰብ ክፍል ከዚህ ሃብት በማትረፍ ከውጪ የሚገቡ የአውሮፓ የቤት እቃዎች እና አዳዲስ አውቶሞቢሎችን በማስመጣት፤ ባንኮችን በማስፋፋትና አዳዲስና በድንጋይ የተገነቡ ቤቶችን በመስራት ከተማዋን ተጠቃሚ አድርገዋል። በ1918 የተሽከርካሪዎች አጠቃላይ መዝገብ 76 ሲሆን በ1922 ወደ 578 ደርሷል። የመጀመሪያው የመንገድ ትራንስፖርት በአዲስ አበባ እና በጅቡቲ መካከል በደሴ አቅጣጫ የተከፈተው አውራ ጎዳና ነው። አውራ ጎዳናው ለጅቡቲው የፈረንሳይ የባቡር መስመር ጠቃሚ ነበር። በ 1922 ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ ጭነው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እና የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ቀጥለዋል ። ከእነዚህም መካከል የኤሌክትሪክ መስመሮችንና ስልክ እንዲሁም እንደ ሚያዚያ 27 አደባባይ ያሉ በርካታ ሐውልቶችን ይካተታሉ። በጣሊያን ወረራ ጊዜ በ1928 ዓ.ም. በጦርነት ጊዜ የፋሺስቶች ሠራዊት ከተማዋን ወርረው ዋና ከተማቸው አደረጉዋት፤ እስከ 1931 ድረስ የኢጣልያ ምስራቅ አፍሪቃ አገረ ገዥ ነበረባት።ከተማዋ ከወረራ በኋላ እስከ 1933 ድረስ የጣሊያን ምስራቅ አፍሪካ ዋና ከተማ ሆና ነበረች። በ1933 ከተማይቱ በሜጀር ጄነራል ዊንጌት እና በአፄ ኃይለ ሥላሴ የኢትዮጵያ ጌዲዮን ሃይል እና የኢትዮጵያ ንቅናቄ ነፃ ወጣች። አፄ ኃይለ ሥላሴም ከሄዱ ከአምስት ዓመታት በኋላ ግንቦት 5 ቀን 1941 ዓ.ም. ተመለሱ። የድህረ-ጣሊያን ወረራ በ1938 አጼ ኃይለ ሥላሴ ከተማዋን የአፍሪካ ዋና ከተማ እንድትሆን ንድፍና እና የማስዋብ ግቦችን ለማሰራት ታዋቂውን እንግሊዛዊ ማስተር ፕላን ሰሪ ፓትሪክ አበርክሮምቢን ጋበዙ። ማስተር ፕላኑ በ1935 ከነበረው የለንደን የትራፊክ ችግር ተሞክሮ በመውሰድ የዋና ዋና የትራፊክ መስመርና የሰፈር ክፍሎችን ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ በመለየት ተጠናቀቀ። ኃይለ ሥላሴ በ1963 በኋላም በ1994 ፈርሶ በአፍሪካ ኅብረት የተተካውን የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰርትም ረድተው ነበር፣ ዋና መሥሪያ ቤቱም በከተማዋ ነው። የተባበሩት መንግሥታት ምጣኔ ሀብት ጉባኤ ለአፍሪቃ ደግሞ ጠቅላይ መሥሪያ ቤት ባዲስ አበባ አለው። በ1957 ዓ.ም. አዲስ አበባ ለኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ስብሰባ ሥፍራው ነበረች። እ.ኤ.አ. በ1957 የተማሪዎች ሰልፍ “መሬት ላራሹ” በሚል መፈክር በማሰማት በኢትዮጵያ የማርክሲስት ሌኒኒስት እንቅስቃሴ ተካሂዷል። በተጨማሪም በ1955 የተከሰተው የነዳጅ ቀውስ በከተማይቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል። በ1966 ዓ.ም ሃይለስላሴ ከስልጣናቸው በፖሊስ አባላት ወረዱ። በኋላም ቡድኑ በይፋ “ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ምክር ቤት” በማለት ራሱን ደርግ ብሎ ሰየመ። በወቅቱ ከተማዋ 10 ወረዳዎች ብቻ ነበሩት። የደርግ አስተዳደር ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ በግምት ሁለት ሶስተኛው ቤቶች ወደ ኪራይ ቤት ተዛወሩ። የህዝብ ቁጥር ዕድገት ከ6.5% ወደ 3.7% ቀነሰ። በ1975 ደርግ በግል ባለ አክሲዮኖች የተገነቡ “ተጨማሪ” የኪራይ ቤቶችን የአገር ንብረት አደረገ። በመሆኑም በአዋጅ ቁጥር 47/1975 የተዳከሙ ቤቶች(ከጭቃ የተገነቡ) በቀበሌ ቤቶች ይተዳደራሉ፣ ጥራት ያላቸው የኪራይ ቤቶች ደግሞ በኪራይ ቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ () ስር ይሆናሉ። እነዚያ የኪራይ ቤቶች ዋጋ ከ100 ብር (48.31 የአሜሪካ ዶላር) በታች ከሆነ በቀበሌ አስተዳደር ሥር ይሆናል። ይህን ተከትሎ የአስተዳደር ክፍፍሉ ወረዳዎች ወደ 25 እና 284 ቀበሌዎች አድጓል። በደርግ ጊዜ የሃንጋሪው አርክቴክት ፖሎኒ በከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር እገዛ የከተማውን ማስተር ፕላን የጀመረው የመጀመሪያው ሰው ነው ፖሎኒ በጊዜው አብዮት አደባባይ ተብሎ የተጠራውን የመስቀል አደባባይን በአዲስ መልክ በመንደፍ ሠርቷል። ኢ.ፌ.ዲ.ሪ (1983-አሁን) ደርግን ለመጣል እየታገለ የነበረው ጥምር ፓርቲ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ግንቦት 20 ቀን 1983 አዲስ አበባን ተቆጣጠረ። ተዋጊዎች 4ኪሎ ቤተመንግስት ታንክና ከባድ መሳርያ ታጥቀው ገቡ። ከአንድ ዓመት በኋላ አዲሱ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት ወጣ። ሁሉም የኢትዮጵያ ከተሞች ተጠሪነታቸው ለክልል አስተዳደር ሲሆን፣ አዲስ አበባ (አዋጅ ቁጥር 87/1997) እና ድሬዳዋ (አዋጅ ቁጥር 416/2004) እራስን በራስ የማስተዳደር እና የልማታዊ ማዕከልነት ስልጣን ያላቸው ቻርተርድ ከተሞች ሆኑ። በሚያዝያ 25/2007 ዓ.ም የአዲስ አበባን ድንበሮች በ1.1 ሚሊዮን ሄክታር ወደ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ለማስፋፋት የተዘጋጀው አወዛጋቢ ማስተር ፕላን፣ የ2007ቱን የኦሮሞ ተቃውሞ አስነስቷል። መንግስት በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ በመተኮስና በድብደባ የሰጠው ምላሽ ወደ ለየለት አድማና ተቃውሞ አባባሰው። አወዛጋቢው ማስተር ፕላን በጥር 12 ቀን 2008 ተሰርዟል።በዚያን ጊዜ 140 ተቃዋሚዎች ተገድለዋል። በአብይ አህመድ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ጊዜ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ "ሸገርን ማስዋብ" የተሰኘ ስራ ተካሂዷል። ይህ ፕሮጀክት የከተማዋን አረንጓዴ ሽፋንና ውበት ለማሳደግ ያለመ ነው። 2010 ዶ/ር አብይ ከእንጦጦ ተራሮች እስከ አቃቂ ወንዝ ድረስ 56 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻዎችን ለማስፋፋት ያቀደውን "የአዲስ አበባ ወንዞች ዳርቻዎች ልማት ፕሮጀክት" የተሰኘ ፕሮጀክት አስጀመሩ። የአዲስ አበባ ከተማ ሠፈሮች ስያሜያቸውን ያገኙት በተለያዩ ምክንያቶችና አጋጣሚዎች ነው። እነዚህንም በተለያዩ ዘርፎች ከፍሎ በቅደም ተከተል ማየት ይቻላል። በርካታዎቹ የከተማዋ ቀደምት ሠፈሮች ስያሜያቸውን ያገኙት በቤተ-መንግሥቱ ዙሪያ መሬት በጉልት መልክ በተሠጣቸው መሣፍንቶችና መኳንንቶች ስም ነው። በዚህ መልክ ስያሜያቸውን ካገኙት ሠፈሮች መካከል ራስ መኮንን ሠፈር፣ ራስ ተሰማ ሠፈር፣ ራስ ብሩ ሠፈር፣ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሠፈር፣ ራስ ስዩም ሠፈር፣ ደጃዝማች ውቤ ሠፈር፣ ነጋድራስ ኃይለ ጊዮርጊስ ሠፈር ፣ ደጃዝማች ዘውዱ አባኮራን ሠፈር እና ሸጎሌ (የአሶሣ ገዢ በነበሩት በሼክ ሆጀሌ አል ሐሠን የተሠየመው) ሠፈር ይጠቀሳሉ። ከእነዚህ ሠፈሮች መካከል ደጃዝማች ውቤ ሠፈር በተለይ ከጣሊያን ወረራ በፊት በሴተኛ አዳሪነት የሚተዳደሩ ነዋሪዎች በከፍተኛ ደረጃ ከሚገኙባቸው የከተማዋ ሠፈሮች አንዱ እንደነበረ ይነገራል። በዚህም ሳቢያ በስነ ቃል በርካታ ግጥሞች በዚህ ሠፈር ዙሪያ ተገጥመዋል። ከነዚህም መካከል፣ «ደጃች ውቤ ሠፈር ምን ሠፈር ሆነች፣ ያችም ልጅ አገባች ያችም ልጅ ታጨች። ደጃች ውቤ ሠፈር ሲጣሉ እወዳለሁ፣ ገላጋይ መስዬ እገሊትን አያለሁ። ደጃች ውቤ ሠፈር የሚሠራው ሥራ፣ጠይሟን በጥፊ ቀይዋን በከዘራ» የሚሉት ይገኙበታል። በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ከመላው የአገሪቱ ማዕዘናት መጥተው አዲስ አበባ በሠፈሩ ብሔረሰቦች የተመሠረቱ ሠፈሮች ይጠቀሳሉ። በዚህ መልክ ከተመሠረቱት ሠፈሮች መካከል ለአብነት አደሬ ሠፈር፣ ጎፋ ሠፈር፣ ወሎ ሠፈር፣ ወርጂ ሠፈር፣ መንዜ ሠፈርና ሱማሌ ተራ ይገኙበታል። የወርጂ ሠፈርን የመሠረቱት የወርጂ ብሔረሰብ አባላት በቆዳና በበርኖስ ንግድ የተሠማሩ እንደነበሩ ይነገርላቸዋል። በተመሣሣይ መልኩ የሱማሌ ተራ ነዋሪዎች ዋነኛ መተዳደሪያ የሻይ ቤት ሥራ እንደነበር ይታመናል። በሶስተኛ ደረጃ በተለያዩ ሙያዎች ተሠማርተው በተለይም በቤተ መንግሥቱ የተለያዩ የሥራ ድርሻዎች በነበራቸው ባለሙያዎች የተቆረቆሩ ሠፈሮችን እናገኛለን። እነዚህም ከብዙ በጥቂቱ ሠራተኛ ሠፈር፣ ዘበኛ ሠፈር፣ ሥጋ ቤት ሠፈር፣ ኩባንያ ሠፈር፣ ጠመንጃ ያዥ ሠፈር፣ ካህን ሠፈር (በኋላ ገዳም ሠፈር) ፣ ገባር ሠፈር ፣ ሠረገላ ሳቢ ሠፈርና ውሃ ስንቁ ሠፈርን ያካትታሉ። ሠራተኛ ሠፈር በአፄ ምኒልክ ቤተ-መንግሥት በዕደ ጥበባት ሙያ በተሠማሩ ነዋሪዎች የተመሠረተ ሠፈር ነው። የሠፈሩ መሥራቾች ዋነኛ ሙያ የብረታ ብረት ሥራ እንደነበረ ይነገራል። ይሄም የተለያዩ የብረታ ብረት ውጤቶችን ለምሣሌ ማረሻ፣ የፈረስ እርካብን፣ የቤት እቃዎችን፣ የጋሻና ጦር እና የጠመንጃ ዕድሳትን ይጨምራል። በቤተ መንግሥቱ በአናጢነት የተሠማሩ ባለሙያዎችም የሚኖሩት በሠራተኛ ሠፈር እንደነበር ይነገራል። በከተማዋ ከሚኖሩት የውጭ ተወላጆችም መካከል ጥቂቶቹ የሚኖሩት በዚሁ ሠፈር ነበር። ከነዚህም የውጭ ነዋሪዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱት አርመናዊው የግብረ ህንፃ ባለሙያ ሙሴ ሚናስ ሔርቤጊን ነበሩ። ዘበኛ ሠፈር የቤተ-መንግሥቱ ጠባቂዎች ወይም የዕልፍኝ ዘበኞች የሠፈሩበት ሠፈር ሲሆን፣ ገባር ሠፈር ደግሞ ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍላተ ሀገር እንደ ማር፣ እህልና ከብት በመሣሠሉት ምርቶች ዓመታዊ ግብር ለመክፈል ወደ ከተማዋ በሚመጡ ግለሰቦች የተመሠረተ ሠፈር እንደሆነ ይነገራል። የውሃ ስንቁ ሠፈር መስራቾች ደግሞ መደበኛ ክፍያ የሌላቸው እና ስንቃቸው ውሃ ብቻ የሆነ የጦሩ አባላት የሠፈሩበት ሠፈር እንደነበረ ይነገራል። በሌላ በኩል ጥቂት የማይባሉ የአዲስ አበባ ሠፈሮች ስያሜያቸውን ያገኙት በተለያዩ አጋጣሚዎች፣ ክስተቶችና ታሪካዊ ክንዋኔዎች ነው። ሠባራ ባቡር ፣ እሪ በከንቱ ፣ ዶሮ ማነቂያ ፣ አፍንጮ በር ፣አራት ኪሎ ፣ ስድስት ኪሎ ፣ አምስት ኪሎ ፣ ጣሊያን ሠፈር፣ ሃያ ሁለት ማዞሪያ፣ ሽሮ ሜዳ እና ነፋስ ስልክ ተብለው የሚጠሩትን ሠፈሮች በዚሁ ዘርፍ መፈረጅ ይቻላል። ሰባራ ባቡር ሠፈር ስያሜውን ያገኘው ሙሴ ሰርኪስ ተርዚያን በሚባሉ አርመናዊ ነጋዴ አማካኝነት ከውጭ አገር መጥቶ አሁን ስያሜውን ባገኘበት ቦታ ተበላሽቶ በቀረው የመንገድ መሥሪያ ተሽከርካሪ (ሮለር) ምክንያት ሠፈሩ ሰባራ ባቡር እንደተባለ ይነገራል። አገሬው “የሠርኪስ ባቡር” እያለ የሚጠራው መሣሪያ አዲስ አበባ በደረሰ ጊዜ የሚከተለው ግጥም ተገጥሞለት ነበር። «ባቡሩ ሰገረ ስልኩም ተናገረ፣ምኒልክ መልአክ ነው ልቤ ጠረጠረ።» በሌላ በኩል ከዐድዋ ጦርነት በኋላ በድል አድራጊው የኢትዮጵያ ሠራዊት የጦር ምርኮኞች የሆኑት የጣሊያን ተወላጆች በማረፊያነት የተመረጠው ቦታ ጣሊያን ሠፈር የሚለውን ስያሜ ማግኘቱ ይታወቃል። እንደዚሁም የስድስት ኪሎ ሠፈር ፣ አራት መንገዶች መገናኛ የሆነው አካባቢ አራት ኪሎ ሠፈር በሁለቱ ሠፈሮች መካከል ያለው አካባቢ ቆይቶ አምስት ኪሎ ሠፈር የሚለውን ስያሜ ማግኘቱም የሚታወቅ ነው። ሌላው በከተማው ከሚገኙ ዋና ዋና ሠፈሮች መካከል በከተማዋ ቀደምት ነዋሪዎች በሆኑት የኦሮሞ ተወላጆችና የቦታ ስሞች የተሰየሙ ሠፈሮችን እናገኛለን። ከነዚህም መካከል ጉለሌ ፣ ጎርዶሜ ፣ ቀበና ፣ ኮተቤ ፣የካ ፣ እንዲሁም ገርጂ እና ላፍቶ የተባሉት ሠፈሮች ለአብነት ይጠቀሳሉ። ከእነዚህም ሠፈሮች መካከል በቀበና ወንዝ ስም በተሰየመው ቀበና ሠፈር ከተገጠሙት ግጥሞች አንዱን እንመልከት። «ቀበና ለዋለ አራዳ ብርቁ ነው፣ አራዳም ለዋለ ቀበና ብርቁ ነው፣እሱስ ላገናኘው ሴት ወይዘሮም ደግ ነው።» በሌላ ዘርፍ ከ1928 የጣሊያን ወረራ እና የአምስት ዓመት ቆይታ ጊዜ አንዳንድ የአዲስ አበባ ቦታዎች እና ሠፈሮች የጣሊያንኛ ስያሜ አግኝተዋል። ከእነዚህም መካከል መርካቶ (የአገሬው ገበያ) ፣ ፒያሣ (የቀድሞው አራዳ) ፣ ካዛንቺስ፣ ካዛ ፖፖላሬ እና ካምቦሎጆ ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ካዛንቺስ ስያሜውን ያገኘው አዲስ አበባ በጣሊያን ይዞታ ስር በነበረችበት ጊዜ ለከፍተኛ የጣሊያን ሹማምንት መኖሪያ ቤቶች በሠራው የጣሊያን ኩባንያ ምህፃረ ቃል ሲሆን ካዛ ፖፖላሬ ደግሞ በዝቅተኛ ደረጃ ለሚገኙ ጣሊያናዊያን ቤቶች በሠራው በካዛ ፖፖላሬ ኩባንያ ስም ነው ስያሜውን ያገኘው። በሌላ በኩል ካምቦሎጆ ሠፈር መጠሪያውን ያገኘው ካምፖ አሎጅዬ ኦፔራ () ከሚለው ስም ሲሆን ይሄም ማለት የሠራተኞች ካምፕ ማለት ነው። እንዲሁም በከተማዋ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያን እና አጥቢያዎች የተሰየሙ ሠፈሮች ሌላው ዋነኛ ዘርፍ ነው። በዚህ ዘርፍ ከሚገኙ ሠፈሮች መካከል ተቀዳሚውን ሥፍራ የሚይዘው አራዳ ጊዮርጊስ ሠፈር ነው። አራዳ በተለይም ከጣሊያን ወረራ ቀደም ባለው ጊዜ የአዲስ አበባ የኢኮኖሚ ማዕከል ከመሆኑ አኳያና በርካታ ማሕበራዊ ክንዋኔዎችን ያስተናግድ የነበረ ሠፈር እንደመሆኑ በስነቃል ብዙ ተብሎለታል። ለአብነት «ሱሪ ያለቀበት አይገዛም አዲስ፣ ወይ አዲስ አበባ ወይ አራዳ ጊዮርጊስ። እስኪ አራዳ ልውጣ ብርቱካን ባገኝ፣ ትናንት ኮሶ ጠጣሁ ዛሬ መረረኝ። ምነው በአደረገኝ ከአራዳ ልጅ መሣ፣ እንኳን ለገንዘቡ ለነፍሱ የማይሣሣ። የአራዳ ዘበኛ ክብሬ ነው ሞገሴ፣በቸገረኝ ጊዜ የሚደርስ ለነፍሴ» የሚሉት ይገኙባቸዋል። በዚህ ዘርፍ የሚመደቡ ሌሎች ሠፈሮች ደግሞ አማኑኤል ፣ ዮሴፍ ፣ ኪዳነ ምሕረት ፣ ቀራኒዮ መድኃኔ ዓለም ፣ እና ቀጨኔ መድኃኔ ዓለምን ያካትታሉ። እ.ኤ.አ. ከ 1888 ዓ.ም. የዐድዋ ጦርነት ድል እና ከአዲስ አበባው ስምምነት በኋላ ጣሊያን፣ ሌሎች የአውሮፓ መንግሥታት እና አሜሪካ የአገራችንን ሉዓላዊነት በመቀበል ከኢትዮጵያ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሥርተዋል። በዚህ ሂደት በርካታ አገሮች የነዚህን አገሮች ፈለግ በመከተል ኤምባሲዎቻቸውን በአዲስ አበባ ከፍተዋል። ከአዲስ አበባ በርካታ ሠፈሮች መካከል አንዳንዶቹ ስያሜያቸውን ያገኙት ከእነዚህ ኤምባሲዎችና ቀደም ሲል ደግሞ ከሌጋሲዮኖች ነው። ፈረንሣይ ሌጋሲዮንና ሩዋንዳ ሠፈሮች ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናቸው። በመጨረሻም ከአዲስ አበባ ሠፈሮች መካከል አንዳንዶቹ በታዋቂ የውጭ አገር ዜጎች ስም የተሠየሙ ናቸው። ከእነዚህም መካከል ቤኒን ሠፈር እና ተረት ሠፈር ይገኙበታል። ቤኒን ሠፈር ስያሜውን ያገኘው ከጣሊያን ወረራ በፊት ተዋቂ ነጋዴ በሆኑት የአይሁድ ተወላጅ ቤኑን ሲሆን ተረት ሠፈር ደግሞ ስያሜውን ያገኘው በአዲስ አበባ ከተከፈቱት ከመጀመሪያዎቹ ሆቴሎች አንዱ በነበረው በሆቴል ዳፍራንስ ባለቤት በሆኑት ፈረንሣዊው ሙሤ ቴረስ ስም ነው። ተረት ሰፈር በጣም ታዋቂ የሆኑ አረብ እመቤት ይኖሩ ነበር ።የሰፈሩ ሰው እኚህን እመቤት <የተረት ሰፈር አድባር> ብሎ ይጠራቸው ነበር : ትክክለኛ ስማቸው ግን ወ/ሮ መርየም ቃሲም ሲሆን የሰፈሩ ሰው ያወጣላቸው የሁልግዜም መጠሪያ ስማቸው ግን "እሜት ማሪያም" ነበር ።የተረት ሰፈር ሰው ሆኖ እሜት ማሪያምን እና የመካሻ ማሞ ጋራጅን የማያውቅ የለም ። ክፍለ ከተሞች አዲስ አበባ በዐሥር ክፍለ ከተሞች እና በዘጠና ዘጠኝ ቀበሌዎች ትከፈላለች። ዐሥሩ ክፍለ ከተሞች ከዚህ በመቀጠል የተዘረዘሩት ናቸው። ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ2012 አስራ አንደኛው የአዲስ አበባ ክፍለ ከተማ ሆኖ ተጨምሯል። የስነ ሕዝብ አወቃቀር በ1999 የኢትዮጵያ ብሄራዊ ስታስቲክስ ባለስልጣናት ባደረገው የህዝብ ቆጠራ አዲስ አበባ በአጠቃላይ 2,739,551 የከተማ እና የገጠር ነዋሪዎች አሏት። ለዋና ከተማው 662,728 አባወራዎች በ628,984 መኖሪያ ቤቶች ውስጥ እንደሚኖሩ ተቆጥሯል, ይህም በአማካይ 5.3 ሰዎች በአንድ ቤተሰብ ማለት ነው።. ሁሉም የኢትዮጵያ ብሔረሰቦች በአዲስ አበባ የሀገሪቱ ዋና ከተማ በመሆኗ የተወከሉ ቢሆንም፣ ትልቁ የአማራ ፣ ተከትሎም ኦሮሞ ፣ እንዲሁም ጉራጌ ፣ ትግራዋይ ፣ ስልጤ ፣ እና ጋሞ ያጠቃልላል። በአፍ መፍቻ ቋንቋነት የሚነገሩ ቋንቋዎች አማርኛ ፣ አፋን ኦሮሞ ፣ ጉራጌኛ ፣ ትግርኛ ፣ ስልጤ እና ጋሞ ይገኙበታል። የኑሮ ደረጃ በ1999 በተካሄደው ሀገር አቀፍ የህዝብ ቆጠራ መሰረት 98.64 በመቶው የአዲስ አበባ መኖሪያ ቤቶች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሲሆኑ፣ 14.9% ንጹህ መጸዳጃ ቤት፣ 70.7% ጉድጓድ መጸዳጃ ቤቶች (አየር ማናፈሻም ያላቸውም ሆነ የሌላቸው) እና 14.3% የሚሆኑት የመጸዳጃ ቤት አገልግሎት አልነበራቸውም። የአዋቂዎች ማንበብና መጻፍ በሀገሪቱ በሁለቱም ፆታዎች ከፍተኛ ሲሆን ለወንዶች 93.6% እና ለሴቶች 79.95% ነው። ከፌዴራል መንግሥት በተገኘው ኦፊሴላዊ አኃዛዊ መረጃ መሠረት በከተማው ውስጥ 119,197 የሚያህሉ ሰዎች በንግድና ንግድ ላይ ተሰማርተዋል; 113,977 በማኑፋክቸሪንግ እና በኢንዱስትሪ; 80,391 የተለያዩ የቤት ሰሪዎች; 71,186 በሲቪል አስተዳደር; 50,538 በትራንስፖርት እና በመገናኛ; 42,514 በትምህርት, በጤና እና በማህበራዊ አገልግሎቶች; 32,685 በሆቴል እና በመመገቢያ አገልግሎቶች; እና 16,602 በግብርና። ከተማዋ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በብዙ ቦታዎች ላይ በረጃጅም ሕንፃዎች ግንባታ ላይ ትገኛለች። የተለያዩ የቅንጦት አገልግሎቶችም እየታዩ ሲሆን የገበያ ማዕከላት ግንባታም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መስሪያ ቤት በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይገኛል። ቱሪዝም በአዲስ አበባ እና በአጠቃላይ በኢትዮጵያ እያደገ ያለ ኢንዱስትሪ ነው። በ2007 የአውሮፓ የቱሪዝም እና ንግድ ምክር ቤት ኢትዮጵያን ለሀገር ውስጥ ቱሪዝም ምርጥ ሀገር ብሎ ሰይሟታል። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና የትግራይ ጦርነት የቱሪዝም ቅነሳ አስከትሏል። በ1987 በወጣው የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የአዲስ አበባ ከተማ ተጠሪነታቸው ለኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት ከሆኑ ሁለት የፌዴራል ከተሞች አንዷ ነች። ቀደም ሲል በ1983ቱ በኢትዮጵያ የሽግግር ቻርተር መሰረት የፌደራል አወቃቀሩን ተከትሎ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወቅቱ ከነበሩት 14 ክልላዊ መንግስታት አንዱ ነበር። ነገር ግን ያ መዋቅር በፌዴራል ሕገ መንግሥት በ1987 ተቀይሮ አዲስ አበባ የክልልነት ደረጃ የላትም። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈጻሚ አካላቱን የሚመራ ከንቲባ እና የከተማውን ደንብ የሚያወጣ የከተማውን ምክር ቤት ያቀፈ ነው። ነገር ግን የፌዴራል መንግሥት አካል እንደመሆኑ መጠን የፌዴራል ሕግ አውጪው በአዲስ አበባ ውስጥ አስገዳጅ የሆኑ ሕጎችን ያወጣል። የከተማው ምክር ቤት አባላት በቀጥታ የሚመረጡት በከተማው ነዋሪዎች ሲሆን ምክር ቤቱ በተራው ደግሞ ከአባላቱ መካከል ከንቲባውን ይመርጣል። ለተመረጡት ባለስልጣናት የስራ ዘመን አምስት ዓመት ነው። ነገር ግን የፌደራሉ መንግስት አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የከተማውን ምክር ቤት እና አጠቃላይ አስተዳደሩን አፍርሶ ምርጫ እስኪደረግ ድረስ በጊዜያዊ አስተዳደር ሊተካ ይችላል። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በፌዴራል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተወክለዋል። ነገር ግን ከተማዋ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አልተወከለችም። በከንቲባው ስር ያለው አስፈፃሚ አካል የከተማውን ስራ አስኪያጅ እና የተለያዩ የሲቪል ሰርቪስ መሥሪያ ቤቶችን ያካትታል። ከ2012 ጀምሮ ከታከለ ኡማ በኋላ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከንቲባ ሆነው በማገልገል ላይ ሲሆኑ፣ በከንቲባነት በመምራት የመጀመሪያዋ ሴት ናቸው።ከታከለ በፊት የፌዴራል መንግስት ከግንቦት 9 ቀን 1998 እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2000 ያገለገሉትን ብርሃነ ደሬሳን በጊዜያዊ ባለአደራ ከንቲባነት እንዲመሩ ሾሟቸው ነበር። የዚህም ምክንያቱ በ1997 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ምርጫ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በአዲስ አበባ ትልቅ ሽንፈት ቢያስተናግድም በአዲስ አበባ ያሸነፉት ተቃዋሚዎች በክልል እና በፌዴራል ደረጃ በመንግስት ውስጥ አልተሳተፉም። ይህ ሁኔታ አዲስ ምርጫ እስኪደረግ ድረስ በኢህአዴግ የሚመራው የፌደራል መንግስት ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመድብ አስገድዶታል። ከቀዳሚዎቹ የአዲስ አበባ ከንቲቦች ፦ አርከበ ዕቁባይ ፣ ዘውዴ ተክሉ ፣ ዓለሙ አበበ እና ዘውዴ ገብረሕይወት ይገኙበታል። ታሪካዊ ምስሎች የውጭ መያያዣ የአዲስ አበባ ካርታ የአዲስ አበባ ካርታ
39424
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%B8%E1%8A%93%E1%8D%8A%20%E1%8A%A8%E1%89%A0%E1%8B%B0
አሸናፊ ከበደ
አስተዳደግና የትምህርት ዘመናት ፕሮፌሶር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ።አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ .)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። በኢትዮጵያ የሥራ አገልግሎት የያሬድ ትምህርት ቤት ዲሬክቶር ሆነው ከ ፲፱፻፶፭ዓ/ም እስከ ፲፱፻፷ ዓ/ም ድረስ ባገለገሉበት ወቅት በንጉሠ ነገሥቱ “ብሔራዊ የሙዚቃ አቀናባሪ” ተብለው ከመሠያማቸውም ሌላ ለባሕላዊ ጉዳዮች ላደረጉት የላቀ ተዋጽዖ በ፲፱፻፶፱ ዓ/ም የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጎ አድራጎት ድርጅት ተሸላሚ ሆነዋል። የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የ፸፭ኛ የልደት በዓል በተከበረበት በዚሁ ዓመተ ምኅረት በሁንጋሪያ መንግሥት ተጋብዘው ወደ ቡዳፔስት በመጓዝ ታዋቂውን «እረኛው ባለዋሽንት» እና «የኢትዮጵያ ሲንፎኒያ” የተባሉትን ሁለት ድርሰቶቻቸውን በአቀናባሪነትና በኦርኬስትራ መሪነት አቅርበው፤ በሸክላ አሳትመዋል። መታሰቢያነቱንም ለጃንሆይ የልደት በዓል አበርክተዋል። ከሸክላው የሚገኘውን ገቢ በወቅቱ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሥር ይተዳደር ለነበረው የመርሐ-ዕውራን ትምህርት ቤት ለግሠዋል። ፕሮፌሶር አሸናፊ ከበደ ‘ጥቁሩ ኮዳሊ’ የሚለውን ማቆላመጫም ያገኙት የረቂቅ ሙዚቃ ድርሰታቸውን በሁንጋሪያ ውስጥ ከ’ፊልሃርሞኒክ ኦርኬስትራ’ው ጋር በሳቸው ሙዚቃ መሪነት ባቀረቡበት ጊዜ ነበር። የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለተመልካቾች ባቀረበው፣ የሕይወት ታሪክ ዳሰሳ ቅንብር ላይ አብሮ አደግ ጓደኛና ሚዜያቸውም የነበሩት፣ ደራሲው አቶ አስፋው ዳምጤ፤ ፕሮፌሶር አሸናፊን ከያሬድ ትምህርት ቤት መልቀቅና ወዲያውም ከአገራቸው ለመሰደድ ያበቃቸው ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ሲሰጡ የተማሪዎች የረቂቅ ሙዚቃ ቅንብር በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ አዘጋጅተው፣ ንጉሠ ነገሥቱ እንዲገኙ በሚኒስትሩ በኩል ያቀረቡት ጥሪ እንደሚደርስ ባለመተማመን በሌላ መንገድ አድርሰው ንጉሠ ነገሥቱ በተገኙበት ለሕዝብ ቀርቧል። ሆኖም በዚህ የተቀየሙት ሚኒስትሮችና የቀጥታ ዓለቆቻቸው በያዙት ቂም እሳቸውን ከዲሬክተርነት አውርደው በምትካቸው አንድ ተራ የክቡር ዘበኛ ባንድ ተጫዋች የነበረ የውጭ ዜጋ አስገቡ። “አገር ትቶ ሲሄድ፤ አይ! እኔ መቼም በገዛ አገሬ ሁለተኛ ዜጋ አልሆንም!” ብሎኛል ይላሉ። በስደት ዘመናት ለከፍተኛ ትምህርት ወደአሜሪካ በተመለሱ ጊዜ የሙዚቃ ጥናታቸውን አጠናቀው፣ የ’ማስተሬት ዲግሪ’ በ፲፱፻፷፩ ዓ/ም፤ በ’ዶክቶር’ነት ደግሞ በ፲፱፻፷፫ ዓ/ም ከ’ዌስሊያን ዩኒቨርሲቲ’ ተመረቁ። ከ ፲፱፻፷፪ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፷፰ ዓ/ም ድረስ በኒው ዮርክ ዩኒቨርሲቲ፣ ‘ክዊንስ ኮሌጅ’ እና በማሳቹሴትስ ብራንዲስ ዩኒቨርሲቲ በረዳት ፕሮፌሶርነት ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ ሕይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ለአሥራ ዘጠኝ ዓመታት በፍሎሪዳ ዩኒቨርሲቲ፤ መጀመሪያ በፕሮፌሶርነትና በኋላም የዩኒቨርሲቲው “የጥቁር አሜሪካውያን የባህል ማዕከል” ዲሬክቶር በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል። በተጨማሪም የዶ/ር መላኩ በያን የአዕምሮ ጥንሥስ የነበረውን “የኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥናትና ምርምር ድርጅት” ዳይሬክቶር በመሆን አገልግለዋል። ፕሮፌሶር አሸናፊ ከመጀመሪያ ሚስታቸው ወይዘሮ ዕሌኒ ገብረመስቀል ጋር ያፈሯቸው ኒና እና ሰናይት የተባሉ የሁለት ሴት ልጆች አባት ሲሆኑ ሰናይት አሸናፊ በአሜሪካ የታወቀች የትዕይንተ-መስኮት ተዋናይ ናት። ሦስተኛ ልጃቸው ያሬድ አሸናፊ ደግሞ ከአሜሪካዊታ ሁለተኛ ሚስታቸው የተወለደ ነው። የሕይወት ፍጻሜ ፕሮፌሶር አሸናፊ ከበደ የ፷ኛ የልደት በዓላቸው ዕለት በመኖሪያ ቤታቸው ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ሞተው የተገኙ ሲሆን፤ ምናልባት የራሳቸውን ሕይወት ሳያጠፉ እንዳልቀሩ ብዙዎች ይገምታሉ። አቶ አበራ ሞልቶት የተባሉት ወዳጃቸው ለኢትዮጵያ ቴለቪዥን ቅንጅት በሰጡት ቃለ-ምልልስ ላይ ከዕለተ ሞታቸው በፊት ጽፈውላቸው እንደነበረና ደብዳቤውንም በመጥቀስ፦ «ጋሽ አበራ፤ ስለዚህ ወረቀት ምን ትላለህ? ይህ አዲሱ ሙከራዬ ነው። ግን እንደራዕይ የሚታየኝ ከመጪው ሐምሌ በፊት ወደሌላ አኅጉር እሄዳለሁ። ሞቼ፣ ሥጋዬን ትቼ ከዚህ ወደኒርቫና እሸጋገራለሁ።» እንደሚል አስረድተዋል። ዘመዳቸው አቶ በቀለ አሳምነው ደግሞ በዚሁ የቴሌቪዥን ቅንብር ላይ ስለዚህ ጉዳይ ሲያብራሩ፦ «“ባባቱ በኩል ታናሽ ወንድም አለው፤ ታዲያ አሸናፊ ወንድሙ ጋ ደውሎ “ከሣምንት በኋላ የለሁም…. ለሰው ልጅ ከስልሳ ዓመት በላይ መኖር ምንድነው ጥቅሙ?» ብሎት ነበር ይሉና ፖሊሶች ከምናየው ሁኔታ የራስን ነፍስ የማጥፋት ድርጊት ይመስላል ማለታቸውን ገልጸዋል። ፕሮፌሶር አሸናፊ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሽልማት ድርጅት ከተቀበሉት ሽልማት ባሻገር የሱዳንን የዳንስ እና የድራማ ኢንስቲቱተ በማቋቋማቸው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሳይንስና የባሕል ድርጅት ሽልማትም ተቀብለዋል። ፕሮፌሶር አሸናፊ ከሙዚቃ ድርሰቶቻቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂነትና ተወዳጅነትን ያተረፈው ‘እረኛው ባለዋሽንት’ ብቻ ሳይሆን ከሌሎቹም አንዳንዱን ለመጥቀስ፦ ‘ሰላም ለኢትዮጵያ’፤ ‘የአገራችን ሕይወት’፤ ‘የተማሪ ፍቅር’፤ ‘እሳት እራት’፤ ‘ኮቱሬዥያ’ እና ‘ኒርቫኒክ ፋንታሲ’ የሚባሉት ድርሰቶች የሚጠቀሱ ናቸው። በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ደግሞ በተማሪነታቸው ዘመን በ፲፱፻፶፮ ዓ/ም የደረሱት እና ያሳተሙት “ንስሐ” ወይም የተባለው መጽሐፍ እና “የሙዚቃ ሰዋሰው” እንዲሁም በርካታ የጥናትና ምርምር ድርሰቶች ይጠቀሳሉ። ዋቢ ምንጮች ፕሮፌሰር ኣሸናፊ ከበደ - የጽሑፎቻቸው ማውጫ የኢትዮጵያ ቴሌቪዝን፤ “የሙዚቃ ሰዎችና ሥራዎቻቸው” ክፍል ፩–፬ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥናትና ምርምር ድርጅት የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች
13066
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%89%E1%8A%AD%E1%88%B0%E1%88%9D%E1%89%A0%E1%88%AD%E1%8C%8D
ሉክሰምበርግ
ሉክሰምበርግ: በኅዳር ፪፻፮ ዓ/ም ዛቪዬ በተል ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆኑ ሉክሳምቡርግ ከቤልጅግና አይስላንድ በኋላ ሦስተኛው ሰዶማዊ የመንግሥት መሪ ያለው አገር ሆነ። በይፋ ሉክሰምበርግ በምእራብ አውሮፓ የምትገኝ በመሬት ተከበበች ሀገር ናት፡፡ በምእራብ እና ሰሜን ከቤልጂየም፣ በምስራቅ ከጀርመን፣ እና በደቡብ ከፈረንሳይ ጋራ ትዋሰናለች፡፡ መዲናዋ ሉክምበርግ ሲቲ ከብሩሰልስ እና ስትራስቦርግ ጋር የአውሮፓ ህብረት፣ የምስራቅ አውሮፓ የፍትህ ፍርድ ቤት፣ የኢዩ ከፍተኛ የህግ አውጪ ባለስልጣን መቀመጫዎች ናቸው፡፡ ባሕሏ፣ ህዝቦቿ እና ቋንቋዋ በከፍተኛ ሁኔታ ከአጎራባች ሐገራት ጋራ በመወራረሱ የተነሳ በዋነኛነት የፈረንሳይ እና የጀርመን ባሕሎች ቅይጥ ሐገር ሆናለች፡፡ ይሄም በሐገሪቱ በሚነገሩ ሶስት አበይት ቋንቋዎች ጉልህ ሆኖ ይቀርባል እነዚህም ሉክሰምበርጊሽ፣ ፈረንሳይኛ፣ እና ጀርመንኛ ናቸው፡፡ በአጎራባች ሐገራት በተለይም በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት ተደጋግሞ የደረሰባት ወረራ የተነሳ ሐገሪቱ በፈረንሳይ እና ጀርመን ድርድር ፈቋዷ እንዲወሰን የሆነ ሲሆን ከብዙ በጥቂቱ የአውሮፓ ሕብረት እንዲመሰረት መሰረቱን ጥሏል፡፡ ስፋቷ 2,586 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ሲሆን (998 ስኩ.ማይልስ) በአውሮፓ ውስጥ ካሉ ሉዐላዊ ሐገራት ውስጥ ትን ግዛት ስትሆን የዩኤስ የሮዴ ደሴትን ያህል ስፋት ወይም የእንግሊዟን ኖርዛምፕተንሻየር ታህላለች፡፡ በ2016 በአውሮፓ ውስጥ በእጅጉ ዝቅተኛ የህዝብ ቁጥር ያላት ሐገር የሚያደርጋት 576,429 ህዝብ ያላት ሲሆን ነገር ግን እስካሁን ከፍተኛው የህዝብ ቁጥር እድገት ምጣኔ ያላት ሐገር ናት፡፡ በህገመንግስታዊ የዘውድ ስርዐት የተወካይ ዴሞክራሲ እነደመኖሩ በከፍተኛው የሉክሰምበርግ መስፍን ከፍተኛ መስፍን ሄነሪ የምትመራ ሲሆን በአለማችን ላይ በመሳፍንት አገዛዛ ስር ያለች ብቸኛ ቀሪዋ ሐገር ናት፡፡ እንደተባበሩት መንግስታት የ2014 መግለጫ ከሆነ ሉክሰምበርግ ያደገች ሐገር ስትሆን ኢኮኖሚዋ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ በአለማችንም ከፍተኛው የነፍስ ወከፍ ምጣኔ ሐብት ያላት ሐገር ናት፡፡ የሉክሰምብግ ሲቲ እድሜ ጠገብ የከተማ ክፍሎቿ እና ምሽጎቿ በ1994 ከፍተኛ ምሽጎችን እና እድሜ ጠገብ ከተማ በልዩ ብቃት ጠብቃ በማቆየቷ የዩኔስኮ የአለም ቅርስ በመሆን ተመዝግባለች፡፡ የሉክሰምበርግ ታሪክ ጀምሯ ተብሎ የሚታሰበው በ963 ባላበት ሲግፍሬድ ባሕረ ሰላጤውን ኮረብታማ መሬት ሲወስድ እና ሉሲሊንቡርሁክ፣ “ትንሽ ግንብ” በመባል የሚታወቀውን የሮማውያን ዘመን ምሽግ፣ እና አካባቢው በቅርቡ ከሚገኘው የንጉሳዊ የቅይዱስ ማክሲሚን ገዳም ከወሰደ በኋላ ጀምሯል፡፡ የሴግፍሬድ ዘሮች ግዛታቸውን በጋብቻ፣ በጦርነት እና በጭሰኛ እና ጌታ ግንኙነት አስፋፍተውታል፡፡ የሉክሰምርግ ባላባቶች በ13ኛው ክፍለዘመን ፍፃሜ ላይ ከፍተኛ ግዛት ላይ መንሰራፋት እና መግዛት ችለዋል፡፡ በ1308 የሉክሰምበርግ ባላባት የሆነው ሄነሪ የጀርመኖች እና የቅዱስ ሮማውያን ንጉሰ ነገስት ንጉስ ሆነ፡፡ የሉክሰምበርግ ተወካዮች ምክር ቤት በመካከለኛው ዘመን አራት ቅዱስ የሮማውያን ንጉሰ ነገስቶችን ሾሟል፡፡ በ1354 ቻርልስ መስተዳድሩን ወደ መሳፍንት ሉክሰምበርግ ቀይሮታል፡፡ ሲጊስሙንድ ወንድ ወራሽ ስላልነበረው መሳፍንቱ ከቡርጉንዲያን በከፊል ሆነዋል እንዲሁም የሐብስቡርግ፣ ኔዘርላንድስ አስራሰባት ግዛተቶች መካከል ሆኗል፡፡ ባለፉት ምዕተ አመታት በፈረንሳይ ንጉሳዊ መንግስት እና በሐብስቡርግ ግዛቶች መካከል የሚገኙት ከፍተኛ ስትራቴጂክ አስፈላጊነት ያላቸው የሉክሰምበርግ ከተማ እና ምሽጎቿ በአውሮፓ ውስጥ በእጅጉ ዝናን ካተረፉ ምሽጎች አንዱ ለመሆን እንዲችሉ ተደርገው የተገነቡ ናቸው፡፡ የፈረንሳዩ ሉዊስ እና የኦስትሪያዋ ማሪያ ቴሬዛ ከተቆጣጠሯት በኋላ ሉክሰምበርግ የመጀመሪያው የፈረንሳይ ሪፐብሊክ እና በናፖሊዎን ስር የነበረው ንጉሳዊ አገዛዝ አካል ሆናለች፡፡ የአሁኗ ሉክሰምበርግ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሐገር ብቅ ያለችው በ1815 በቪዬና ኮንግረስ ወቅት ነበር፡፡ ከሐይለኛ ምሽጎቹ ጋር ከፍተኛው መስፍን ከተማዋን በፈረንሳይ ከሚሰነዘርባት ሌላ ወረራ ለመከላከል ከፕሩሲያን ሽምቅ ተዋጊዎች ጋራ በኔዘርላንድሱ ዊሊያም የግል ቁጥጥር ስር በመሆን ነጻ እና ገለልተኛ ሐገር ሆናለች፡፡ በ1839 ከቤልጂየም አብዮት መፈንዳት በኋላ ፈረንሳይኛ ብቻ የሚናገረው የሰሉክሰምበርግ አካል ወደቤልጂየም ተቀላቅሏል እና ሉክሰምበርጊሽ ተናጋሪው ክፍል የአሁኗን ሉክምሰምበርግ መስርተዋታል፡፡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የቀዩን ምድር የበለፀገ ብረታዘል መሬት የብረት ኢንዱስትሪው ፍለጋ ባደረገበት ወቅት ሐገሪቱን ወደኢንዱስትሪ ግስጋሴ ውስጥ አስገብቷቷል፡፡ ዋና መስሪያ ቤቱን በሉክሰምበርግ ከተማ ያደረገው የአለማችን ታላቁ የብረት አምራች የሆነው አርሴሎርሚታል አሁንም እነዚህን ወቅቶች የሚያስታውሰን ነው፡፡ በ1960ዎቹ የብረት ኢንዱስትሪው ውድቀት ካስመዘገበ በኋላ የአለማችን የገንዘብ ማዕከል ፣ለመሆን ሐገሪቱ ራሷን በማደራጀቱ ላይ ትኩረቷን በማድረግ አሁን የታወቀችበትን የባንክ ማዕከል ለመገንባት ችላለች፡፡ ከ21ኛው ክፍለ ዘመን ጅማሬ አንስቶ መንግስቶቿ ሐገሪቱን በእውቀት ወደታነጸ ኢኮኖሚ ልማት ውስጥ በማስገባቱ ላይ ያተከረች ሲሆን ከዚህም ጋራ ተያይዞ የሉሰምበርግ ዩንቨርስቲ እና ብሔራዊ የህዋ ፕሮግራም በ2020 ወደጨረቃ በሚደረግ ሰው አልባ ጉዞ ላይ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ለማድረግ በማቀድ መስርታለች፡፡ ሉክሰምበርግ የአውሮፓ ህብረት፣ ኦኢሲዲ፣ የተባበሩት መንግስታት፣ ናቶ፣ እና ቤኔሉክስ መስራች አባል ስትሆን የፖለቲካ ስምምነቷን በኢኮኖሚ፣ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ውህደት ላይ መስርታለች፡፡ የሐገሪቱ መዲና እና ትልቋ ከተማ የሆነችው የሉክሰምበርግ ሲቲ የአውሮፓ ህብረት በርካታ ተቋማት እና ኤጀንሲዎች መቀመጫ ናት፡፡ የሐገሪቱ የመጀመሪያው ታሪክ ሆኖ በተመዘገበው ሉክሰምበርግ በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በ2005 እና 2006 አገልግላለች፡፡ በ2016 የሉክሰምበርግ ዜጎች ወደ 172 ሐገራት እና ግዛቶች ነጻ ቪዛ ወይም በደረሱበት ቪዛ እንዲሰጣቸው ሆኖ የነበረ ሲሆን ካናዳ እና ስዊትዘርላንድ ከመሳሰሉ ሐገራት ጋራ በተያያዘ የሉክሰምበርጋዊን ፓስፖርት በአለም 6ኛው በመሆን ደረጃ ተሰጥቶታል፡፡ የሉክሰምበርግ ታሪክ መመዝገብ የጀመረው በሲግፍሪድ፣በአርዴኔስ ኮርት የሚገኘው እድሜ ጠገብ ቋጥኝ ያለው ሉሲሊንቡሩህክ (የዛሬው የሉክሰምበርግ የንጉሳዊያን መኖሪያ) በመያዝ፣ የንጉሳዊው የቅይዱስ ማክሲሚን ገዳም ልውውጥ በ1955 እ.ኤ.አ. በማድረግ ነው፡፡ በዚህ ምሽግ አካባቢ ከተማ በሂደት መመስረቱን በመቀጠል ከፍተኛ ስትራቴጂክ ጠቀሜታ ያለው ማዕከል መሆን ችሏል፡፡ የመሳፍንት ግዛት በ14ኛው እና 15ኛው ክፍለ ዘመናት ሶስት የሉክሰምበርግ ምክር ቤት አባላት የሮማ ቅዱሳት ነገስታት በመሆን ነገሱ፡፡ በ1437 እ.ኤ.አ. የሉክሰምበርግ ምክር ቤት በዙፋኑ ላይ የሚቀመጥ ወንድ በማጣት የአልጋ ወራሽ ችግር ገጥሞት ነበር፣ ይኸውም ግዛቶች በደቿ ኤልሳቤጥ ለቡርገንዲው ፊሊፕ እንዲሸጥ አድርጓል፡፡ በሚከተሉት ምዕተ አመቶች የሉክምበርግ ምሽግ ተከታትለው በመጡ ሰፋሪዎቿ፣ ቦርቦኖች፣ ሐብስበርጎች፣ ሆሄንዞለርንስ እና ፈረንሳዮች ከጊዜ ወደጊዜ ሰፍቷል እንዲሁም ተጠናክሯል፡፡ አስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን ናፖሊዎን በ1815 እ.ኤ.አ. ከተሸነፈ በኋላ፣ ሉክሰምበርግ በፕሩሺያ እና በኔዛርላንድስ መካከል ክርክር እንዲፈጠርባት ምክንያት ሆናለች፡፡ ከኔዘርላንድስ ጋራ በሕብረት በመሆን በጀርመን ኮንፌዴሬሽን ውስጥ የቪዬና ኮንግረስ ሉክሰምበርግን እንደትልቅ መሳፍንት አመራር በማድረግ የመሰረታት ሲሆን፣ በዚሁ ጊዜ የኔዘርለንድስ አካል በመሆን እና እንደአንድ ግዛቷ በመሆን እየተመራች የሉክሰምበርግ ምሽጎች በፕሩሺያ ጦር ሰራዊት ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ይሄ ስምምነት በለንደኑ የ1839 እ.ኤ.አ. የመጀመሪያው ስምምነት የተከለሰ ሲሆን ከዚሁ እለት በኋላ የሉክሰምበርግ ሙሉ ነጻነት ከ1830-1839 እ.ኤ.አ. የቤልጂየም አብዮት በተነሳበት ወቅት ዕውን የሆነ ሲሆን እና በ1839 እ.ኤ.አ. ስምምነት ሙኑ ነፃነቷን ተቀዳጅታለች፣ የሉክሰምበርግ ግዛት ከግማሽ በላይ የተቀነሰ ሲሆን፣ በብዛት የፈረንሳይኛ ተናጋሪ የሆነው ምዕራባዊው የሐገሪቱ ክፍል ወደቤልጂየም ተዛውሯል፡፡ በ1842 እ.ኤ.አ. ሉክሰምበርግ የጀርመንን የጉምሩክ ሕብረት (ዞልቨሬይን) ተቀላቅላለች፡፡ ይኸውም የጀርመን ገበያ እንዲከፈት፣ የሉክሰምበርግ የብረት ኢንዱስትሪ እንዲያድግ፣ እና የሉክሰምበርግ የምድር ባቡር ኔትወርክ ከ1855 እስከ 1875 እ.ኤ.አ. ድረስ እንዲስፋፋ፣ በተለይም ከዚህ አንስቶ የአውሮፓውያንን የኢንዱስትሪ ክልሎች የሚያገናኘው የሉክሰምበርግ-ቲዎንቪል የባቡር ሐዲድ እንዲገነባ አድርጓል፡፡ አሁንም የፕሩሺያ የጦር ሰራዊት ምሽጎቹን ተቆጣጥረዋቸው ስለነበር በ1861 እ.ኤ.አ. ፓሰሬል ተከፈተ፣ ቪል ሆትን እና በቦክ የሚገኙትን ዋና ምሽጎች ከሉክሰምበርግ የምድር ባቡር ጣቢያ ጋር የሚያገናኘው የፔትሩስ ወንዝ ሸለቆን የሚያቋርጠው የመጀመሪያው የመንገድ ላይ ድልድይ፤በደቡብ አቅጣጫ በሚገኘው በዚያ ወቅት በተመሸገው ቡርቦን ሜዳማ ክፍል ላይ በ1959 እ.ኤ.አ. ተከፈተ፡፡ በ1866 ከተከሰተው የሉክሰምበርግ ችግር በኋላ በፕሩሺያ እና ፈረንሳይ መካከል ጦርነት የተፈጠረ ሲሆን፣ ከፍተኛው የመሳፍንት ነጻነት እና ገለልተኝነት በ1867ቱ እ.ኤ.አ. በለንደኑ ሁለተኛው ስምምነት በድጋሚ ተረጋግጧል፣ የፕሩሺያ የጦር ሰራዊት ከሉክሰምበርግ ምሽጎች በመውጣት ቦክ እና በአቅራቢያው የሚገኙ ምሽጎች ፈራርሰዋል፡፡ የኔዘርላንድስ ንጉስ የሉክሰምበርክ ከፍተኛ መስፍን ርዕሰ ብሔር በመሆን የቀጠለ ሲሆን፣ እስከ 1890 እ.ኤ.አ. ድረስ በሁለቱ ሐገራት መካከል ያለውን የሁለቱን ሐገራት ግንኙነት አስቀጥሏል፡፡ ዊሊያም ከዚህ አለም በሞት ሲለይ የኔዘርላንድስ ዙፋን ወደሴት ልጁ ዊልሔልሚና ተላለፈ፣ በዚህም ሁኔታ ሉክሰምበርግ (በናሱ ቤተሰብ ፓክት በወንድ ወራሾች ብቻ ተወስኖ የነበረው) ወደናሱ-ዌይልበርጉ አዶልፍ ተላልፏል፡፡ በ1870 እ.ኤ.አ. በፍራንኮ-ፕሩሺያን ጦርነት ጊዜ ወታደሮችን ከሜትዝ (በመቀጠል ጠፈረንሳይ ክፍል የሆነችው) በመሳፍንቱ ሐገር እንዲያልፉ ፈረንሳይ የባቡር ሐዲዱን መጠቀሟን አስመልክተቶ እና ወደቲዎንቪል አቅርቦቶችን ለማቅረብ ምንም እንኳን ክርክሮች የነበሩ ቢሆንም፣ የሉክሰምበርግ ገለልተኛነት በጀርመን አክብሮት ተቸሮታል፣ እና ጀርመንም ሆነች ፈረንሳይ ሀገሪቱን ወረዋት አያውቁም፡፡ ነገር ግን በ1871እ.ኤ.አ. ጀርመን በፈረንሳይ ላይ ድል በመቀዳጀቷ ሜትዝ እና ቲዎንቪልን ጨምሮ ሉክሰምበርግ ከሎሬን ጋራ ያላት ድንበር ከፈረንሳይ ጋራ ከመጎራበት ይልቅ በፍራክፈርት ስምምነት መሰረት እንደአልሴስ-ሎሬን ከጀርመን ንጉሳዊ መንግስት ጋራ ወደተያያዘችው ተለውጧል፡፡ ይሄም ጀርመን የባቡር ሐዲዶችን የመቆጣጠር እና የማስፋፋት ወታደራዊ ጥቅም እንድታገኝ አስችሏታል፡፡ ሐያኛው ክፍለ ዘመን ኦገስት 1914 እ.ኤ.አ. ንጉሳዊቷ ጀርመን ከፈረንሳይ ጋራ ባደረገችው ጦርነት በሉክሰምበርግ ላይ ወረራ በማካሄድ የሉክሰምበርግን ገለልተኝነት ጥሳለች፡፡ ይሄ ሁኔታ ጀርመን የባቡር ሐዲዱን መጠቀም እንድትችል አድርጓቷል፡፡ በዚሁ ሁኔታ ከፈረንሳይ ነጥቃዋለች፡፡ ይሁንና ከጀርመን ሰፈራ ባሻገር ሉክሰምበርግ አብዛኛውን ነጻነቷን እና የፖለቲካ ስልቶቿን እንድታስቀጥል ሁኔታዎች ተመቻችተውላታል፡፡ በ1940 እ.ኤ.አ. የ ኛው የአለም ጦርነት ከተነሳ በኋላ የናዚ ጀርመን ዌህርማችት ወደሐገሰሪቱ በገባ ጊዜ የሉክሰምበርግ ገለልተኛነት በድጋሚ “ሙሉ ለሙሉ ያለማብራሪያ” ተጣሰ፡፡ ከመጀመሪያው የአለም ጦርነት በተቃርኖ በሆነ መንገድ በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት ጀርመን በሉክሰምበርግ መስፈሯ ሐገሪቱን የጀርመን ግዛት ተደርጋ እንድትቆጠር አድርጓታል እና ቀጥተኛ ባልሆነ መልኩ በትይዩ ከምትገኘው ከሶስተኛዋ ሬይች አውራጃ ጋር እንድትያያዝ አድርጓታል፡፡ መቀመጫውን በለንደን አድርጎ የነበረው በስደት ላይ የነበረው መንግስት አጋሮችን በመደገፍ በኖርማንዲ ወረራ ላይ ተሳታፊ የሆኑ በጎ ፈቃደኛ አናሳ ቡድኖችን ልኮ ነበር፡፡ ሉክሰምበርግ በሴፕቴምበር 1944 እ.ኤ.አ. ነጻ የወጣች ሲሆን በ1945 እ.ኤ.አ. የተባበሩት መንግስታት መስራች አባል ሆናለች፡፡ በህገመንግስቱ የሉክሰምበርግ ገለልተኛ አቋም በ1948 ያበቃ ሲሆን በ1949 እ.ኤ.አ. የናቶ መስራች አባል ሐገር ሆናለች፡፡ በ1951 ከስድስቱ የአውሮፓውያን የድንጋይ ከሰል እና የብረት ማሕበረሰብ አንዷ የሆነች ሲሆን ይኸውም ማሕበረሰብ በ1957 እ.ኤ.አ. የአውሮፓውያን የኢኮኖሚ ማሕበረሰብ የሆነው እና በ1993 እ.ኤ.አ. የአውሮፓ ሕብረት የሆነው ሕብረት ሲሆን እንዲሁም በ1999 እ.ኤ.አ. ሉክሰምበርግ የዩሮ መገበያያ አካባቢን ተቀላቅላለች፡፡ በ2005 እ.ኤ.አ. ለአውሮፓ ህገመንግስት በሚመሰርተው የአሕ ስምምነት ላይ ህዝበ ውሳኔ ተካሂዷል፡፡ ሉክሰምበርግ በህገመንግስታዊ የዘውድ አገዛዝ የሚመራ የፓርላማ ዲሞክራሲ ያላት ሐገር ናት፡፡በ1868ቱ እ.ኤ.አ. ህገመንግስት የህግ አስፈጻሚነት ስልጣን በከፍተኛው መስፍን እና በርካታ ሌሎች ሚኒስቴሮችን በያዘው ካቢኔው ተይዞ ነበር፡፡ ከፍተኛው መስፍን የህግ ረቂቅን የማፍረስ አቅም የነበረው ሲሆን በዚህ ሁኔታ አዲስ ምርጫ በሶስት ወራት ጊዜ መከናወን ነበረበት፡፡ ይሁንና ከ1919 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሐገሪቷ ሉዐላዊነት ሰፈነ፣ በህገመንግስቱ እና በህጉ መሰረት በከፍተኛ መስፍኑ ይተገበራል፡፡ የህግ ማውጣት ስልጣን ለዲኤታው ምክር ቤት፣ ከአራት የመራጮች አካላት ለአምስት አመት የስልጣን ዘመን ለተመረጡ ስልሳ አባላት ላሉት በአንድ የህግ አውጭው አካል ለተዋቀረው የህግ አውጪ ተሰጥቷል፡፡ ሁለተኛው አካል፣ የሐገሪቱ ምክር ቤት (ኮንሴይል ድኢታት) በከፍተኛው መስፍን የተመረጡ ሐያ አንድ መደበኛ ዜጎችን የያዘ ሲሆን የህግ ረቂቆችን በማርቀቁ ሂደት የዲኤታዎችን ምክር ቤት ያማክራል፡፡ ከፍተኛው መስፍን ሶስት የስር ፍርድ ቤቶች ያሉት ሲሆን (ጀስቲስ ደ ፔይክስ፣ በኢስች-ሱር-አልዜቴ፣ የሉክሰምበርግ ከተማ እና ዲየኪርች)፣ ሁለት አውራጃ ፍርድ ቤቶች (ሉክሰምበርግ እና ዲየኪርች) እና የፍትህ ከፍተኛ ፍርድ ቤት (ሉክሰምበርግ)፣የአቤቱታ ፍርድ ቤቱን እና የሰበር ሰሚ ችሎትን ይጨምራል፡፡ በተጨማሪም አስደተዳደራዊ ችሎት እና አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት ያለ ሲሆን እንዲሁም የህገመንግስቱ ፍድ ቤት ሁሉም በመዲናዋ ይገኛሉ፡፡ አስተዳደራዊ መምሪያዎች ሉክሰምበርግ በ12 የአስተዳደር ክፍሎች የተከፈለች ሲሆን በ105 ትንንሽ የአስተዳደር ክፍሎች በተጨማሪም ተከፍለዋል፡፡ አስራሁለቱ ትንንሽ አስተዳደሮች የከተማ ደረጃ ያላቸው ሲሆን ከእነዚህ መካከል ሉክሰምበርግ ከተማ ትልቋ ነች፡፡ የውጭ ግንኙነት ሉክሰምበርግ ለረጅም ዘመን የአውሮፓ ፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ ውሕደትን በዋነኛነት ስትደግፍ ቆይታለች፡፡ የአውሮፓን ውሕደት በሚተነብየው ጥረታቸው ሉክሰምበርግ እና ቤልጂየም በ1921 እ.ኤ.አ. የቤልጂየም-ሉክሰምበርግ የኢኮኖሚክ ሕብረትን የመሰረቱ ሲሆን ይሄም ልውውጥ የሚደረግበት መገበያያ ገንዘብ ለመፍጠር እና የጋራ እሴት እንዲኖር ያለመ ነበር፡፡ ሉክሰምበርግ የቤኔሉክስ የኢኮኖሚ ሕብረት አባል እና የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማሕበረሰብ (አሁን የአውሮፓ ሕብረት) አባል ናት፡፡ በተጨማሪም በሸንጀን ቡድን ውስጥ (ስምምነቱ በተፈረመባት የሉክሰምበርግ መንደር ስም የተሰየመ) የተሳተፈች ሲሆን፣ ግቡም በአባል ሐገራት መካከል የሚደረግ ነፃ ዝውውር ማለት ነው፡፡ በዚሁ ጊዜ አብዛኛው የሉክሰምበርግ ዜጎች የአውሮፓ ሕብረት ስሜት የሚኖረው በፍተኛ የትራንስ አትላንቲክ ግንኙነት ግንዛቤ ውስጥ እና ፕሮ-ናቶ፣ ፕሮ-ዩኤስ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲን የሚከተል ይሆናል፡፡ ሉክሰምበርግ የአውሮፓውያን የፍትህ ፍርድ ቤት፣ የአውሮፓ አዲተሮች ፍርድ ቤት፣ የአውሮፓ ሕብረተሰብ የስታቲስቲክ ጽ/ቤት (“ዩሮስታት”) እና ሌሎች አስፈላጊ የኢዩ አካላት መቀመጫ ናት፡፡ የአውሮፓ ፓርላማ ሴክሬተሪያት በሉክሰምበርግ የሚገኝ ሲሆን ነገር ግን ፓርላማው በአብዛኛው የሚሰበሰበው በብሩሰልስ እና አልፎ አልፎም በስትራስቡርግ ነው፡፡ ሉክሰምበርግ በመከላከያ ሐይሉ እና በናቶ ውስጥ በጅጉ አነስተኛ የሆነ የጦር ሰራዊት ያላት ሲሆን እስከ 800 የሚጠጉ ወታደሮች እና 100 የመንግስት ሰራተኞች ናቸው፡፡ በየብስ የተከበበች ሐገር እንደመሆኗ የባሕር ሐይል የላትም፡፡ ሉክሰምበርግ በተጨማሪም የአየር ሐይል የሌላት ሲሆን፣ ይሁንና የናቶ 17 ኤደብሊውኤሲኤስ አውሮፕላኖች እንደሁኔታዉ የሉክሰምበርግ አውሮፕላኖች ሆነው ተመዝግበዋል፡፡ ከቤልጂየም ጋራ ባደረገችው የጣምራ ስምምነት ሁለቱም ሀገራት ለአንድ ኤ400ኤም ወታደራዊ ካርጎ አውሮፕላን የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ መልክዐ ምድር ሉክሰምበርግ በአውሮፓ አንዷ እጅግ ትንሽ ሐገር ናት እንዲሁም የአለማችን 194 ነጻ ሐገራት በስፋቷ 179ኛ በመሆን ተቀምጣለች፡፡ ሐገሪቱ በስፋቷ 2,586 ስኩዌር ኪሎሜትር (998 ስኩ. ማ) ስትሆን እንዲሁም ርዝመቷ 82 ኪሜ (51 ማይ) እና 57 ኪሜ (35 ማ) ወርድ አላት፡፡ በ490 እና 510 ሰ ላቲቲውድ እና 50 እና 70 ምስ ሎንግቲውድ መካከል ትገኛለች፡፡ በምስራቅ ሉክሰምበርግን የጀርመን የቡንደስላንድ ሪኔላንድ-ፓላቲኔት እና ሳርላንድ ሲያዋስናት እና በስተደቡብ የፈረንሳይዋ ክልል ሎሬይን ታዋስናታለች፡፡ ታላቋ የመስፍን ሐገር የቤልጂየሟ ዋሉን ክልል የምትዋሰን ሲሆን፣ በተለይ ኋላ የተመለከተችው የሉክሰምበርግ ግዛት እና ሊዬጅ፣ ከፊሎቹ ጀርመንኛ ተናጋሪ የቤልጂየም ማሕበረሰብን ያቀፈ ሲሆን፣ በምዕራብ እና በሰሜን በተከታታይ ናቸው፡፡ የሐገሪቱ ሰሜናዌ ሩብ ክፍል “ኦዬስሊንግ” በመባል የሚታወቁ ሲሆን እና የአርዴኔስ ግማሽ ክፍል ናቸው፡፡ ኮረብታማ እና ዝቅተና ተራሮችን የያዘ ሲሆን የክኔይፍ አቅራቢያ ዊልዌርዴጅ፣ ከፍታ ላይ የሚገኘውን ነጥብ፣ በ560 ሜ (1,837 ጫማ) ነው፡፡ ሌሎች ተራሮች “ቡርግፕላዝ” 559 ሜትሮች ሁልዳንጅ አካባቢ እና “ናፖሌዎንስጋርድ” በ 554 ሜትሮች ራምብሮች አካባቢ ናቸው፡፡ ክልሉ በተራራቀ መልኩ ህዝብ የሰፈረበት ሲሆን አራት ሺህ በላይ በሚደርስ ህዝብ ባለበት አንድ ከተማ ብቻ ይገኛል (ዊልትዝ)፡፡ የሐገሪቱ ደቡባዊ ሁለት ሶስተኛ ክፍል “ጉትላንድ” በመባል የሚጠራ ሲሆን ከኦየስሊግ ይልቅ ህዝብ ተጠጋግቶ የሚኖርባት አካባቢ ናት፡፡ በተጫሪም ይበልጥ ብዝሐነር ያላት እና በአምስት የመልክዐምድር ክፍሎች የምትከፈል ናት፡፡ የሉክሰምበርግ አምባ በደቡብ ማዕከላዊ ሉክሰምበርግ ሰፊ፣ ዝርግ፣ አሸዋማ ድንጋ የሚበዛባት ቦታ እንዲሁም የሉክሰምበርግ ከተማ ሳይት ናት፡፡ ከሉክሰምበርግ ምስራቅ አቅጣጫ ትንሷ ስዊትዘርላንድ ኮረብታማ ገፅታ እና ጥቅቅ ያሉ ደኖች ያሉበት ስፍራ ነው፡፡ የሞሴል ሸለቆ ዝቅተኛው ቦታ ሲሆን በደቡባዊው ምስራቅ ድንበር ታኮ የሚሄድ ቦታ ነው፡፡ ሬድ ላንድስ በደቡባዊው ጫፍ እና በደቡባዊው ምዕራብ የሉክሰምበርግ የኢንዱስትሪ ልብ እና የሉክሰምበርግ ትልልቅ ከተሞች መገኛ ቦታ ነው፡፡ የሉክሰምበርግ እና የጀርመን ድንበር ላይ ሶስት ወንዞች ያሉ ሲሆን እነዚህም ሞሴል፣ ሳውየር፣እና ኦውር ናቸው፡፡ ሌሎች አበይት ወንዞች አልዜት፣ ክሌርቭ፣ እና ዊልትዝ ናቸው፡፡ የሳውር መካከል እና አተርት ሸለቆ በጉትላንድ እና ኦዬስሊንግ ድንበር መካከል ነው፡፡ በ2012 እ.ኤ.አ. የአካባቢ ደረጃ መጣኝ መሰረት ሉክሰምበርግ በአካባቢ ጥበቃ ምዘና ከተደረገባቸው 132 ሐገራት መካከል በደረጃ አራተኛዋ የተሻለች ፈጻመሚ ናት፡፡ በሜርሰርስ ከወጡት ለመኖ የሚመቹ ምርጥ 10 ሐገራት መካከል ሉክሰምበርግ 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ አየር ንብረት ሉክሰምበርግ የባሕር አይነት የአየር ንብረት ያላት ሲሆን (ኮፐን፡ ሲኤፍቢ)፣ በተለይ በክረምት መገባደጃ ከፍተኛ ዝናብ ይኖራታል፡፡ ክረምቶች ዋቃት እና በጋዎች ቀዝቃዛ ናቸው፡፡ ሉክሰምበርግ አመቺ የሆነ የመንገድ፣ የባቡር እና የአየር ትራንስፖር ፋሲሊቲዎች እና አገልግሎቶች አሏት፡፡ የመንገድ ኔትወርክ በቅርብ አመታት በጉልህ ዘመናዊ ሲሆን 147 ኪሜ (91ማይ) የሞተር መንገዶች መዲናዋን ከአጎራባች ሐገራት ጋራ ያገናኟታል፡፡ ከፍተኛ ፍጥነት ያለው ፓሪስ ድረስ የሚያገናኘው የቲጂቪ አገናኝ መምጣት የከተማዋ የባቡር ጣቢያ እንዲታደስ ያደረገ ሲሆን እና በ2008 እ.ኤ.አ. በሉክሰምበርግ አየር ማረፊያ አዲስ የተሳፋሪዎች ተርሚናል ተከፍቷል፡፡ በመዲናዋ የከተማ የኤሌክትሪክ ባቡር እንዲሁም ቀላል ባቡር በአቅራቢያ አካባቢ ዎች በቀጣይ ጥቂት አመታት የማስተዋወቅ እቅድ አለ፡፡ በሉክሰምበርግ በ1000 ሰዎች 680.1 ተሽከርካሪዎች አሉ ይኸውም ከሁለቱ የሞናኮ መስተዳድር እና የብሪቲሽ የውጭ ግዛት ከሆነችው ጂብራልታር በስተቀር ከሁሉም በላይ ነው፡፡ በሉክሰምበርግ የቴሌኮሙኒኬሽን ኢንዱስትሪ ከፓለቲካ ተፅዕኖ ነጻ ሲሆን እና የኤሌክትሮኒክ ኔትወርኮች በጉልህ ደረጃ አድገዋል፡፡ በተለያዩ ኦፕሬተሮች መካከል ያለው ውድድር በ2011እ.ኤ.አ. በወጣው ፓኩዌት ቴሌኮም የመንግስት የህግ ረቂቅ ማዕቀፍ ዋስትና ተሰጥቷቸዋል ይኸውም የአውሮፓውያንን የቴሌኮም መመሪያዎች ወደሉክሰምበርግ ህግ የተለወጠ ነው፡፡ ይኸውም የኔትወርክ እና አገልግሎቶችን ኢንቨስትመንት ያበረታታል፡፡ ተቆጣጣሪው አይኤልአር- ኢንስቲቱት ሉክሰምቦርጂስደ ሬጉሌሽን ለማሕበራቱ በእነዚህን ደንቦች ተገዢ እንዲሆኑ ማረጋገጫ ያቀርባል፡፡ የሉክሰምበርግ ህዝብ ሉክሰምበርጋዊያን በመባል ይታወቃሉ፡፡ ከቤልጂየም ፣ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ጀርመን እና ፖርቱጋል አብዛኞቹ በኋላ ላይ ከተጠቀሰው መጡ ሆነው በመበራከታቸው የተነሳ በ20ኛው ክፍለ ዘመን ስደተኛ ህዝብ በቅጥር እድገት አሳይቷል፡፡ በ2013 እ.ኤ.አ. የፖርቱጋል ዜግነት ያላቸው 88,000 ነዋሪዎች ነበሩ፡፡ በተጨማሪም ጥቂት የሚባሉ የሮማኒ (ጂፕሲ) እና የአይሁድ ህዝቦች አሉ፡፡ ሁለቱ በሉክሰምበርግ የሚኖሩ ማህበረሰቦች ከፍተኛ ጭፍጨፋ ደርሶባቸው ከሉክሰምበርግ እንዲወጡ ሆኗል፡፡ ከዩጎዝላቭ ጦርነት ጅማሬ አንስቶ ሉክሰምበርግ ከቦስኒያ እና ሄርዞጎቪና፣ ሞንቴኔግሮ፣ እና ሰርቢያ በርካታ ስደተኞችን አስተናግዳለች፡፡ በአመት ከ10,000 በላይ አዳዲስ ስደተኞች ወደሉክሰምበርግ ይደርሳሉ፣ አብዛኞቹም ከአሕ ሐገራ ናቸው እንዲሁም አምስራቅ አውሮፓ ናቸው፡፡ በ2000 እ.ኤ.አ. በሉክሰምበርግ 162,000 ስደተኞች በሉክሰምበርግ ነበሩ እነዚህም የህዝብ ቁጥሩን 37 በመቶ ይሆናሉ፡፡ በሉክሰምበርግ በግምት 5,000 ህገወጥ ስደተኞች በ1999 ነበሩ፡፡ በሉክሰምበርግ ሶስት ቋንቋዎች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡ እነዚህም ፈረንሳይኛ፣ ጀርመን፣ እ ሉክሰምበርጊሽ ሲሆኑ የሞስሌ ክልል ፍራንኮኒያን ቋንቋ በቤልጂየም፣ ፈረንሳይ እና ጀርመን አጎራባች ክፍሎች ይነገራል፡፡ ምንም እንኳን ሉክሰምበርጊሽ የጀርመን ምዕራብ ማዕከላዊ ከፍተኛ የጀርመን ቋንቋዎች ቡድን ቢሆንም ከ5000 በላይ የሆኑ የቋንቋው ቃላት መሰረታቸው ከፈረንሳይኛ ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ የታተሙ የሉክሰምበርጊሽ አረፍተ ነገሮች በሳምንታዊው “ሉክሰምበርገር ዎቼንብላት” ጋዜጣ ሁለተኛው እትም በአፕሪል 14 1821 እ.ኤ.አ. ላይ ይታሉ፡፡ ከሶስቱ አንዱ ይፋዊ ቋንቋ እንደመሆኑ ሉክሰምበርጊሽ የከፍተኛው መስፍን ብሔራዊ ቋንቋ እንደሆነ ይቆጠራል፡፡ እያንዳንዳቸው ሶስቱ እንደዋነኛ ቋንቋ በመሆን በተወሰኑ ሁኔታዎች ጥቅም ላይ ይውላሉ፡፡ የሉክሰምበርግ የትምህርት ስርአት በሶስት ቋንቋ የተዘጋጀ ነው፡ የመጀመሪያዎቹ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት አመታት በሉክሰምበርጊሽ ሲሆኑ፣ ወደጀርመን የሚቀየር ሲሆን፣ በሁለተኛ ደረጃ የመማር ማስተማሩ ቋንቋ ወደፈረንሳይኛ ይለወጣል፡፡ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመመረቅ በሶስቱ ቋንቋዎች ብቁ ሆኖ መገኘት ያስፈልጋል፡፡ በትምህርት ቤት እንግሊዝኛ ትምህርት የሚሰጥ በመሆኑ በተለይ በሉክሰምበርግ ሲቲ ሰዎች እንግሊዝኛ መናገር ይችላሉ፡፡ ፈረንሳይኛ የመንግስት ተመራጭ ቋንቋ ነው፡፡ ሉክሰምበርግ ሐይማኖትን የማትቀበል ሐገር ናት ሆኖም ሐገሪቱ የተወሰኑ ሐይማኖቶችን በይፋ ሁሉም ሊከሉት የሚገባ ሐይማኖት በማድረግ እውቅና ይሰጣል፡፡ ይሄ ሐገሪቱ በሐይማኖት ላይ የማስተዳደር እና ካሕናትን በመምረጡ ረገድ ሚና እንዲኖራት ያስችላል፣ ለዚህም በተለዋጭ የተወሰኑ የስራ ማስኬጃ ወጪዎችን እና ምንዳ ይከፍላል፡፡ ከ1980 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግስት በሐይማኖታዊ እምነቶች ወይም ልማዶች ላይ ስታቲስቲክስ መሰብሰቡ ህገወጥ ነገር ሆኖ ቆይቷል፡፡ በሲአይኤ ፋክትቡክ ግምት መሰረት በ2000 እ.ኤ.አ. ዓመት 87% ሉክሰምበርጎች የንጉሳዊያን ቤተሰቦችን ጨምሮ ካቶሊኮች ሲሆ፣ ቀሪዎቹ 13% ሙስሊሞች፣ ፕሮቴስታንቶች፣ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች፣ አይሁዶች፣ እና ሐይማኖት የለሾች ናቸው፡፡ በ2010 ፒው የምርምር ማዕከል ጥናት መሰረት 70.4% ክርስቲያኖች፣ 2.3% ሙስሊሞች፣ 26.8% ምንም ዝንባሌ የሌላቸው፣እና 0.5% ሌሎች ሐይማኖቶች ናቸው፡፡ የሉክሰምበርግ ዩንቨርሲቲ እና የሉክሰምበርግ ሚያሚ ዩንቨርሲቲ ግቢዎች ሉክሰምበርግ ውስጥ የሚገኙ ሁለት ዩንቨርሲቲዎች ናቸው፡፡ ሉክሰምበርግ በአውሮፓ ውስጥ በነፍስ ወከገፍ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን አልኮል ትሸጣለች፡፡ ይሁንና ከአጎራባች ሐገራት ደንበኞች የሚገዛው ከፍተኛ ቁጥር ያለው አልኮል በስታቲስቲክስ በነፍስወከፍ ከፍተኛ የአልኮል ሽያጭ ሲሆን ይሄ የአልኮል ሽያጭ ደረጃ የሉክሰምበርግ ህዝብን ትክክለኛ የአልኮል ሽያጭ አይወክልም፡፡ ሉክሰምበርግ በጎረቤቶቿ ባሕል ተሸፍና ቆይታለች፡፡ በርካታ ባሕሎች አሏት በርካታዉ ሕብረተሰብ በገጠራማው ክፍል የሚኖር ነው፡፡ በአብዛኛው በመዲናዋ የሚገኙ በርካታ ታዋቂ ሙዚየሞች አሏት፡፡ እነዚህም የታሪክ እና ስነ-ጥበብ ብሄራዊ ሙዚየም፣ የሉክሰምበርግ ከተማ ታሪክ ሙዚየም፣ እና አዲሱ ከፍተኛው መስፍን ጂን የዘመናዊ የስነ-ጥበብ ሙዚየም (ሙዳም) ናቸው፡፡ በዲየኪርች የሚገኘው የብሔራዊ ወታደራዊ ታሪክ ሙዚየም የቡልጅ ታሪክን በመወከሉ በልዩ ሁኔታ ይታወቃል፡፡ የሉክሰምበርግ ከተማ ራሷ በምሽጎቿ ታሪካዊ አስፈላጊነት ረገድ በዩኔስኮ የአልም ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ገብታለች፡፡ ሐገሪቱ የተወሰኑ በአለማቀፍ ደረጃ የታወቁ ከያኔያን ያሏት ሲሆን እነዚህም ሰዐሊው ቴዎ ኬርግ፣ ጆሴፍ ኩተር እና ሚሼል ማጄሩስ እና በዩኔስኮው የአለም መዝገብ ትውስታ ላይ የሰው ዝርያ በሚል የተቀመጠለት የፎቶግራፍ ባለሞያው ኤድዋርድ ስቴይቼን እና አሁን በክሌርቫውክስ በቋሚነት የሚገኘው ነው፡፡ የፊልም ኮከብ የሆኑት ሎሬታ ያንግ የሉክሰምበርጊሽ ዝርያ ያላቸው ግለሰብ ናቸው፡፡ ሁለት ጊዜ የአውሮፓ የባሕል መዲና በመባል የተሰየመች ጀየመጀመሪያዋ ከተማ ናት፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1995 እ.ኤ.አ. ነው፡፡ በ2007 የአውሮፓ የባህል መዲና የሉክሰምበርግን ከፍተኛ መስፍን ሬይንላንድ-ፕፋልዝ እና በጀርመን የምትገኘውን ሳርላንድ፣ የዋሉን ክልልን እና ጀርመንኛ ተናጋሪ የሆነውን የቤልጂየም ክፍል እና በፈረንሳይ የሚገኘውን ሎሬን ክልል አካታ ድንበር ተሻጋሪ ሆናለች፡፡ በአውሮፓ ካሉት በርካታ ሐገራት በተለየ መልኩ የሉክሰምበርግ ስፖርት በአንድ ብሔራዊ ስፖርት ላይ የተወሰነ አይደለም ነገር ግን ቡድን እና በግል በርካታ ስፒርቶችን ያካትታል፡፡ ከ521,353 ሕዝቧ 10,000 የአንደኛው ወይም የሌላኛው ስፖርት ፌዴሬሽን ፈቃድ ለው አባ ነው፡፡ ትልቁ የሐገሪቱ የስፖርት ማዕከል ድኮክ የሚሰኘው በሉክሰምበርግ ሰሜናዊ ምስራቅ አቅጣጫ በኪርችበርግ የሚገኘው የቤት ውስጥ ሜዳ እና የኦሎምፒክ መዋኛ ገንዳ ሲሆን 8300 ሰዎችን መያዝ ይችላል፡፡ ሜዳው ለቅርጫት ኳስ፣ ለእጅ ኳስ፣ ጂምናስቲክ፣ እና የመረብ ኳስ ሜዳዎችን የሚያካትት ነሲሆን የ2007 እ.ኤ.አ. የአውሮፓ የሴቶች መረን ኳስ የፍጻሜ ጨዋታን ጨምሮ አ ስተናግዷል፡፡ ታዋቂ የስፖርቱ ሰዎች፡ · አልፓይን ስኪየር ማርክ ጊራርዴሊ ከ1985 እና 1993 እ.ኤ.አ. መካከል ለአምስት ጊዜ የአለም ዋንቻ አጠቃላይ ሻምፒዮና · ሳይክሊስት ኒኮላስ ፍራንትዝ፣ የ1927 እና 1928 እ.ኤ.አ. ቱር ደ ፍራንስ አሸናፊ፣ ቻርሊ ጋውል የ1956 እና 1959 እ.ኤ.አ. ጊሮ ደኢታሊያን እና በ1959 እ.ኤ.አ. የቱር ደ ፍራንስ አሸናፊ፣ ኤልሲ ጃኮብስ፣ በ1958 እ.ኤ.አ. የመጀመሪያዋ የሴት የመንገድ የአለም ሻምፒዮን፣ እና አንዲ ሽሌክ የ2010 ቱር ደ ፍራንስ አሸናፊ፡፡ · የመካከለኛ ርቀት ሯጭ ጆሲ ባርቴል፣ በ1952 እ.ኤ.አ. የክረምት ኦሎምፒክ የወንዶች 1500 ሜትር አሸናፊ፡፡ · 1961 እ.ኤ.አ. የአለም የውሐ ስኪ ሻምፒዮን ሳይልቪ ሁልሴማን · የቴኒስ ተጫዋች ጊልስ ሙለር፣ አን ክሬመር እና ማንዲ ሚኔላ የሉክሰምበርግ ምግብ በላቲን እና በጀርመን አለማት መካከል ያለውን ድንበር የሚያንጸባርቅ ሲሆን በአጎራባች ፈረንሳይ እና ጀርመን ምግቦች በከፍተኛ ሁኔታ ተፅዕኖ አድሮበታል፡፡ የሉክሰምበርግ ሚዲያ አበይት ቋንቋዎች ፈረንሳይኛ እና ጀርመንኛ ነቸው፡፡ ሰፊ ስርጭት ያለው ጋዜጣ በጀርመን ቋንቋ የሚወጣው የዕለት ሉክሰምበርግ ወርት ነው፡፡ ፖርቱጊውዝ እና እንግሊዝኛ የራዲዮ እና ብሔራዊ የህትመት ሚዲያዎች አሉ፡፡ ሉክሰምበርግ በራዲዮ እና በቴሌቪዥን ጣቢያዎቿ በመላው አውሮፓ ትታወቃለች፡፡ ሉክሰምበርግ በሚስተር ሁብሎት አማካኝነት አኒሜትድ ፊልም ዘውግ በ2014 እ.ኤ.አ. የኦስካር አሸናፊ ሆናለች፡፡ በተጨማሪም የሚከተሉትን ይመልከቱ · የሉክሰምበርግ ማውጫ · የሉክሰምበርግ አርክቴክቸር · በሉክሰምበርግ የንጉሳውያን መኖሪያዎች ዝርዝር · የሉክሰምበርግ ሐይቆች · የውጭ ዕዳ ያለባቸው ሐገራ ዝርዝር የአውሮፓ አገራት
50108
https://am.wikipedia.org/wiki/Love%2C%20Simon
Love, Simon
(እንግሊዝኛ)(በአማርኛ "ከፍቅር ጋር፣ ሳይመን") 2018 እ.አ.አ የተለቀቀ በ በተጻፈው በተባለው መጽሐፍ መሰረት በ የተዘጋጀ አሜሪካዊ የፍቅርና ወጣት ኮሜዲ-ድራማ ፊልም ነው። ዋና ዋና ተዋናዮቹ እና ናቸው። የፊልሙ ጭብጥ የሚያጠነጥነው ሳይመን ስፒየር () በተባለ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ላይ ነው። ሳይመን እራሱን ይፋ ያላወጣ የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪ ሲሆን ይህም እንዳይታወቀብት ሚስጥሩን ከቤተሰቡና ጓደኞቹ እንዲሁም ማንነቱን ለትምሕርት ቤት ሊያጋልጥው ካስፈራራው ሰው ጋር የሚያደርገውን ትግል ያሳያል። በተጨማሪም በበይነ መረብ ከተዋወቀው እና ፍቅር ካስያዘው ነገር ግን ማንነቱን የማያውቀውን የክፍል ጓደኛው ማን እንደሆን ለማወቅ የሚያደርገውንም ጥረት ያሳያል። መጀመሪያ የታየው ፌብሪወሪ 27፣ 2018 እ.አ.አ በ ሲሆን በይፋ የተለቀቀው በዩናይትድ ስቴትስ ማርች 16 2018 እ.አ.አ ነው። የፊልም ተቺዎች በበኩላቸው ፊልሙ ባሉት "ደማቅ የፍቅር ስሜት፣ ለየት ለየት ያለ የተዋናዮች ቡድንና አብዮታዊ መደበኛነት" አሞግሰውታል። በተጨማሪም ፊልሙን "አስደሳችና ልብ የሚነካ" መሆኑን ገለጸዋል። በስመ ጥር የሆሊውድ ስቱዲዮ የተሰራ የመጀመሪያው በተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪ ወጣት የፍቅር ሕይወት ታሪክ ላይ ያተኮረው ፊልም በዓለም ዙሪያ $65 ሚሊዮን ብር ገቢ አስገኝቷል። ሳይመን ስፒየር በአትላንታ፣ ጆርጂያ ክፍለ ከተማ የሚኖር የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪነቱን ያልገለጸ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ነው። ከቤተሰቡ ጋር ጠንካራና በፍቅር የተሞላ ግንኙነት አለው። አስቀድሞ የሚያውቃቸው ኒክ () እና ሊያ () እንዲሁም ቅርብ ጊዜ ከተዋወቃት አቢ () ጋር ጥብቅ ጓደኝነት መስርቷል። አንድ ቀን ሊያ ሳይመንን የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች የምስጢር መስጫ ድረ ገጹ ላይ በድብቅ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪ ስለሆነው አንድ የትምህርት ቤታቸው ተማሪ ጽፎ ስላየችው ጽሁፍ ትነገረዋለች። ስለተማሪው የሚታወቀው በኦንላይን ስሙ "" (ብሉ) መባሉ ብቻ ነው። ሳይመን በኢሜይል ከብሉ ጋር መጻጻፍ ይጀምራል፣ እርሱም ለኢሜይሉ "" (ዣክ) የሚል ስም ይጠቀማል። ሁለቱም ስለራሳቸው ግላዊ መረጃ በመለዋወጥ ግንኙነት ይፈጠራሉ። ይሁን እንጂ እርስ በእርሳቸው የተላላኳቸው ኢሜይሎች በስህተት በሌላ ተማሪ እጅ ይገባል። የሳይመንን ሚሰጢር በእጁ ያስገባው ማርቲን () የሚባለው ተማሪ አቢን የሳይመን ጓደኛ በጣም ይወዳታል ነገር ግን ጓደኛ ሊያደርጋት አልቻለም። የሳይመንን ምስጢር እንደ ማስፈራሪያ በመጠቀም አቢን ጓደኛው እንድትሆን እንዲረዳው ይህን ካላደረገ ግን ምስጢሩን ለመላው ትምህርት ቤት እንደሚነግርበት አስፈራራው፡፡ ሳይመን በዚህ መሃል የክፍል ጓደኛው የሆነው ብራም () "ብሉ" ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ ይጀምራል። በሃሎዊን ግብዣ ላይ ሳይመን ከብራም ጋር ለመነጋገር ቢሞክርም ከሴት ተማሪ ጋር ሲሳሳም ያየዋል። ሳይመን ለኒክ አቢን የሚወድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ የሆነ የፍቅር ጓደኛ እንዳላት በመንገር ይዋሸዋል። ከግብዣው በኋላ ሊያ ለሳይመን አንድን ሰው እስከ ሕይወቷ መጨረሻ የምታፈቅር ሆኖ እንደሚሰማት ትነግረዋለች። ሳይመን ይህ የምታፈቅረው ሰው ኒክ ነው ብሎ ያምናል። በአንድ ምግብ ቤት ውስጥ ሳይመን ከአቢና ከማርቲን ጋር ተገናኝቶ ለሚያሳዩት የቲያትር ትዕይንት ይለማመዳሉ። ከሳይመንና ከአስተናጋጃቸው፣ ላይል ()፣ በመሃል ጥሩ ግንኙነት ይፈጠራል። ሳይመን እርሱ "ብሉ" ሊሆን ይችላል ብሎ ያምናል። በኋላ በሌሊት ሳይመን ለአቢ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪነቱን ይነግራታል። እርሷም በአዎንታዊ ስሜት ትቀበለዋለች። በትምህርት ቤት የኳስ ጨዋታ ላይ ሆነው ሳይመን ላይልን ያየዋል። ላይል "ብሉ" መሆኑን ሊጠይቅ እያሰበ ሳለ ግን ላይል አቢን እንደሚወድ ይደርስበታል። በዚህም የተናደደው ሳይመንን ማርቲን ምክር እንዲሰጠው ሲጠይቅ ሳይመን አዝወትሮ መነዝነዙ አበሳጭቶት "ደፍረህ የፈለግከውን አድርግ ወይም ተወው" ይለዋል። በዚህ መሰረት ማርቲን ያቀደውን ለማድረግ ይወስናል። ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት ተሳታፊዎች ሁሉ ብሔራዊ መዝሙር መዘመራቸውን ማርቲን ያስቆማና ለአቢና ለተሳታፊዎች ሁሉ አቢን እንደሚወድ ይነግራቸዋል። አቢ ግን ለእርሱ እንደዚያ ዓይነት ስሜት እንደሌላት ትነግረዋለች። ይህንንም ተከትሎ ማርቲንን ሌሎቹ ተማሪዎቹ ያላገጡበታል። ማርቲን በተፈጠረው ነገር ሰዎች እርሱ ላይ ማላገጣቸውን እንዲያቆሙና በበቀል ስሜት በገና ዋዜማ የሳይመን ኢሜይሎችን በምስጢር ድረ ገጹ ላይ በመለጠፍ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪነቱን ለመላው ትምህርት ቤት ያሳውቅበታል። የሳይመን እህት ኖራ () ወንድሟን ልታጽናናው ብትሞክርም ፍቃደኛ ሳይሆን በመቅረት የመኝታ ቤቱ በር ይዘጋባታል በዚህም ብቻ ሳያበቃ ከትምህርት ቤት ጓደኞቹ ለሚደርሱት መልዕክቶች ምላሽ መስጠት ያቆማል። በዕለተ ገና ሳይመን የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪነቱን ለወላጆቹ ይነግራቸዋል። ምንም እንኳ ቢገርማቸውም ይቀበሉታል። ከበዓል ዕረፍት በኋላ ፍቅረኛሞች የሆኑት ኒክ እና አቢ ተበሳጭተው ሳይመንን ስለ ነገራቸው ውሸቶች ያፋጥጡታል። እርሱም ያደረጋቸውን ነገሮች በሙሉ ማርቲን እያስፈራራው የሰራቸው ጥፋቶች መሆኑን ይነግራቸዋል። ሊያ የምትወደው ኒክን ሳይሆን ሳይመን መሆኑን ትነግረዋለች። ጓደኞቹ ከተጣሉት በኋላ ሳይመን ከብሉ የመጨረሻ ኢሜይል ይደርሰዋል። በኢሜይሉ ውይይታቸው ብሉ ይፋ በመውጣቱ ማዘኑን ይገልፃል። ከዚያህ በኋላም መጻጻፋቸውን መቀጠል እንደማይፈልግ ነግሮ የኢሜይል መለያውን ያስወግዳል። ሳይመን ጓደኞቹን ብቻ ሳይሆን ፍቅር ያስያዘው ምስጢራዊውን ሰው ስላጣ በጣም ያዝናል። በትምህርት ቤት መመገቢያ ክፍል ውስጥ ሳይመንን እና ግልጽ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪ የሆነ ኢታን () በተባለ ሌላ ተማሪ ላይ ሁለት ተማሪዎች ያላገጣሉ። በሳይመን እና በኢታን መካከል የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪነታቸውን መግለጻቸውን ተከትሎ ያጋጠሟቸውን ችግሮች በመወያየት ጥሩ ግንኙነት ይፈጠራሉ። ሳይመን ሊያን ይቅርታ ይጠይቃታል። በምስጢር መስጫ ድረ ገጹ ላይ ጓደኞቹን በይፋ ይቅርታ ይጠይቃቸዋል እንዲሁም ብሉ ከእርሱ ጋር የትምህርት ቤት ካርነቫል በዓል ላይ እንዲገናኙ ይጠይቀዋል። ከትምህርት ቤቱ የሙዚቃ ዝግጅት በኋላ ሊያ፣ ኒክ እና አቢ ከሳይመን ጋር እርቅ ያወርዱና ከእነርሱ ጋር ወደ ካርነቫሉ እንዲሄድ ይጋብዙታል። ሳይመን ብሉን ለመጠበቀ ፌሪስ መንኩራኮሩ ላይ ይቀመጣል። ሳይመን የፌሪስ መንኩራኮር ላይ ለመቆየት የገዛቸው ትኬቶች በሙሉ ሲያለቁ ማርቲን ላጥፋው ጠፋት ካሳ ሌላ አንድ ዙር ትኬት ለሳይመን ይገዛለታል። ዙሩ ከመጀመር በፊት ብራም ከሳይመን ጎን በመቀመጡ ብሉ እርሱ መሆኑን ለሁሉም ግልጽ ያደርጋል። ሳይመን ከሴት ተማሪ ሲሳሳም ያየው በስካር መንፈስ የተሰራ ስህተት እንደነበረ ይነግረዋል። አንድ ላይ ፌሪስ መንኩራኮሩ ላይ ተቀምጠው ይሳሳማሉ ይሄንንም ክስተት ቆመው ሲመለከቱ የነበሩት ጓደኞቻቸው ደስታቸውን በጨብጨባ ይገልጣሉ። የሳይመን ሕይወት ቀስ በቀስ ወደ ቀድሞ ሁኔታው ይመለሳል። እርሱና ብራም ፍቅረኛሞች ይሆናሉ። የአሜሪካ ፊልሞች
40341
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A3%E1%8B%AB%E1%8A%93%20%E1%89%A5%E1%88%A9
ኣያና ብሩ
ኢንጂነር ኣያና ብሩ የአማርኛ የጽሕፈት መሣሪያንና በመሣሪያው የኣከታተቡን ዘዴ የፈጠሩ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው። ከኣድዋ ድል በኋላ ኢትዮጵያውያን የእንግሊዝኛውን የታይፕራይተር ወይም የጽሕፈት መሣሪያ ኣጠቃቀም ከተረዱ ወዲህ መሣሪያውን ለኣማርኛ ቀለሞች እንዲያገለግል ለ85 ዓመታት ግድም ቢታገሉም ሳይሳካ ቀርቷል። በመካከሉ ከተደረጉት የተለያዩ ሙከራዎች መካከል የኢንጂነር ኣያና ሥራ ኣንዱ ነበር። ዋናውም ችግር የመሣሪያው መርገጫዎች በኣማርኛ ፊደላት መብዛት የተነሳ በቂ ስለኣልነበሩ ፊደላቱን ከተለያዩ መርገጫዎች በመሰብሰብ በመቀጣጠል የሚያስከትብ ዘዴ ወደ ፲፱፻፳፭ ዓ.ም. ግድም ኣቀረቡ። በእዚህ ዘዴ “ሀ” ከኣንድ መርገጫ ከተከተበ በኋላ “ሁ” ፊደል የሚከተበው “ሀ” ጎን የመቀነስ ምልክትን ወይም “-” በማስቀመጥ ነበር። ይኸንኑ የመቀነስ ምልክት “ለ”፣ “ሐ”፣ “መ” እና የመሳሰሉት ጎን በማስቀመጥ “ሁ”፣ “ሉ”፣ “ሑ”፣ “ሙ” ስለሚመስሉ ኣንዱኑ መቀጠያ ለተለያዩ የፈጠራ ቁርጥራጮች እንዲሆን ተደረገ። እንደነ “ሹ” የመሳስሉትን በቅጥልጥል ለመክተብ ከ“ሰ” እና የመቀነስ ምልክት የተሠራውን “ሱ” ፊደል በሌላ መርገጫ ቀደም ብሎ ወይም ወደኋላ መልሶ ሌላ ረዥም መሰመር ከሌላ መርገጫ ከ“ሰ” ኣናት ላይ በማስቀመጥ ነበር የሚሠራው። ይህ የቅጥልጥል ፊደል ኣሠራርና መኖር ዓማርኛ ባልሆነ ነገር ቀለሞቹን በመሰሉ ነገሮች የቢሮ ሥራ መሥራት ስለተቻለ ኣያና ብሩ ለኢትዮጵያ ታላቅ ባለውለታ ናቸው። የኣያና መሣሪያ ባይኖር ኖሮ የቢሮ ጽሑፎችን በእጅ ጽሑፍ ተጠቅሞ መቀጠል ማዛለቁ ስለሚያጠራጥር ኢንጂነር ኣያና ለዓማርኛ እድገት ክፍተኛ ኣስተዋጽዖ ኣድርገዋል። እንዲህም ሆኖ ትክክለኛውን የግዕዝ ቀለሞች የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ቀደም ብለው ሲጠቀሙባቸው ስለነበርና በኋላም ሲጠቀሙበት ስለነበረ የታይፕ ፊደል ከማተሚያ ቤቶቹ ጋር ግንኙንት ኣልነበረውም። የኣያና የጽሕፈት መኪና ቀለሞችም የዓማርኛ ፊደላት ኣልነበሩም፤ ሊሆኑም ኣይችሉም። ይህ ልዩነት ያልገባቸውና ከመቶ ያነሱ መርገጫዎች ላይ የተበተኑትን የታይፕ ቁርጥራቾጭ ከ፪፻ በላይ የሆኑት የዓማርኛ ቀለሞች ኣንድ የሚመስሏቸው ዛሬም ኣሉ። የኢንጂነሩ የጽሕፈት መኪና ፊደል እንደ እንግሊዝኛው ወደ ኮምፕዩተር መግባት ነበረበት የሚሉ ቢኖሩም የእንግሊዝኛው ቅጥልጥል ስላልሆነና ትክክለኛዎቹን ቀለሞች ስለከተበ ነው ወደ ኮምፕዩተር የተሻሻለው። የዓማርኛው መሣሪያ ግን ዓማርኛ ስላልከተበ ወደ ኮምፕዩተር መግባት የለበትም ብለው በጽሑፍ ተከራክረው ያስቀሩት ዶ/ር ኣበራ ሞላ ናቸው። ከእዚህም ሌላ የዓማርኛ መሣሪያው ብዙ ችግሮች ኣሉት። ለምሳሌ ያህል ያልተሟላ ከመሆኑ ሌላ የገጹ ስፋት ወይም የፊደሉ መጠን ሲቀየር ቅጥሎቹ ይገነጠላሉ ወይም ይደበቃሉ። ማሕተም የመሳሰሉትን ለመሥራት ሲሞከር ቅጥሎቹ ኣንዳንድ ስፍራዎች ይዘው ስለሚቀመጡ ኣያሠሩም። የቀለሞቹ ኣመዳደብና ኣከታተብ ለመቀጠል ማመቸት ላይ የተመሠረተ ነው። ፊደላቱ ሲቀጠሉ ኣስቀጣይና ተቀጣይ ኣስቀያሚ ኣዳዲስ መልኮች እንዲኖሯቸው ኣስገድዷል። በተጨማሪም የታይፕ መሣሪያው ዓላም ጽሑፍን ወረቀት ላይ ለማስፍር ብቻ ሲሆን የኮምፕዩተር ጥቅም ኮዶቹን ማስቀመጥ ነው። የጽሕፈት መሣሪያው ውሱን ኣሠራር በኣንድ የፊደል መጠን እንዲሠራ ሲሆን ኮምፕዩተር ኣንዱን ፊደል ለተለያዩ የፊደል መጠኖችና ቅርጾች የሚያሠራ ነው። የታይፕ መጻፊያው በኣንድ የላቲን የፊደል ገበታ ምትክ የቀረበ ስለሆነ ጊዜው የኣለፈበት መሣሪያ ነበር። ዶክተሩ ግዕዙን ወደ ኮምፕዩተር የኣስገቡት በስምንት የእንግሊዝኛ የፊደል ገበታዎች ምትክ መሆኑ ታትሟል። መሣሪያው ተሻሽሎም ሊጠቅም ስለማይችልና ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች ሊያስከትብ ስለማይችል ወደ ኮምፕዩተር አንዳይገባ በምክንያት ቀርቧል። በምትኩ ትክክለኛዎቹን የግዕዝ ፊደላት ወደ ኮምፕዩተር በዶክተሩ ኣዲስ ዘዴ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥራ ላይ ውሏል። በእዚህ የተነሳ ወደ ዩኒኮድ የዓለም ፊደላት መደብ የገባው ትክክለኛው የግዕዝ ፊደል ስለሆነ በዓማርኛ ታይፕራይተር ቁርጥራጭ ፊደላት መጠቀም ከቀረ ቆይቷል። ዶክተሩ የአማርኛ ታይፕራይተየር ኣማርኛን እንዳልጻፈ ስለሚያውቁ እንጂ ቀደም ብለው የታይፑን ዓይነት ማውጣት ስለሚችሉ ሁሉንም የዓማርኛ ቅጥልጥሎች የሚያስከትብ ፊደል ለመጀመሪያ ጊዜ ሠርተው ሰዉ ስለ ኤድስ እንዲያነብበት በነፃ ለግሰዋል። የኣማርኛ ታይፕራይተር ከኣንድ የፊደል ገበታ የመቀጣጠል ዘዴ እ.ኤ.ኣ. ከ1985 ጀምሮ በኮምፕዩተርም ቀርቦ ነበር። ግዕዝ በዶ/ር ኣበራ ሞላ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ የታይፕራይተሩ ዘዴ ውድቅ ቢሆንም ይኸን ከኣቀረቡትም ኣንዱ ግዕዝ ያልሆነውን በሓሰት ነው ከማለቱም ሌላ ፓተንት ኣለኝ የሚል ኢትዮጵያዊ ኣለ። ዶክተሩ እየተቃወሙም እ.ኤ.ኣ. በ1992 ለዩኒኮድ የቀረበ የተሻሻለ የታይፕ መሣሪያ ቅጥልጥል ፊደል እዚህ ኣለ። ዶክተሩ የዓማርኛ ፊደላት ተቀጣጥለው ለኮምፕዩተር ኣይቀርቡም ብለው ከኣሸነፋ በኋላ ሌሎች እ.ኤ.ኣ. በ1996 ትክክኛዎቹን የዓማርኛ፣ ትግርኛና ኦሮምኛ ቀለሞች ኣቅርበው የኣናሳ ቋንቋዎች የግዕዝ ፊደላት መብዛት የኣልፈለጉ መንደርተኞች በቅጥልጥልነት ዩኒኮድ መደብ ውስጥ እንዲገቡ የፈለጉትንም ኣሸንፈው ዛሬ ወደ 500 የሚጠጉ የግዕዝ ቀለምች በተነጣጠል በዩኒኮድ ዕውቅና ኣግኝተዋል። ይህ ሁሉ ሲደረግ እያንቀላፉ ከኣሉት መካከል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምሁራንና ሌሎችም ኣሉበት። ኢንጂነር ኣያና ብሩ ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረችበት ጊዜ ኣርበኛ ነበሩ። የውጭ መያያዣዎች ስለ አማርኛ ፊደል መሻሻል የተደረጉ ጥናቶች መዘርዝር፣ ክንፈ ሚካኤል፣ ፳፻፪ ዓ.ም.፣ ሜልበርን፣ ኦስትሬልያ ኣበራ ሞላ የኢትዮጵያ ሰዎች
46347
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B5%E1%8A%95%E1%89%A2%E1%89%B0%20%E1%8B%B3%E1%8A%95%E1%8A%A4%E1%88%8D
ትንቢተ ዳንኤል
ዳንኤል የሚለው ስም "ዳን" እና "ኤል" የሚሉት የሁለት ቃላት ጥምረት ሲሆን ትርጓሜውም እግዚአብሔር ፈራጄ ወይም ዳኛዬ ነው ማለት ነው፡፡ ዳንኤልና ሦስቱ ወዳጆቹ የአይሁዳውያን ማኅበረሰብ ክፍል የነበሩና ወደ ባቢሎን በምርኮ እንደ ተወሰዱ መጽሐፉ ያትታል (ዳን1)፡፡ ዳንኤል በባቢሎን በነበረበት ጊዜ ብልጣሶር የሚል ተጨማሪ ስም ነበረው፡፡ በባቢሎናውያን ቋንቋ ብልጣሶር ማለት "ሕይወቱን ጠብቀው" ማለት ነው፡፡ ነቢዩ ዳንኤል በይሁዳ አገር ከመሳፍንት ወይም ከንጉሣዊ ቤተሰብ የተወለደ፣ የባቢሎንና የፋርስ ሥልጣኔ እጅግ በጣም ባየለበትና ዓለም በእነዚህ ሥልጣኔዎች በተወረረችበት ጊዜ የኖረ ሰው ነው፡፡ ዳንኤል በወቅቱ ከነበሩት ታላላቅ ነገሥታት ከሚባሉት ከእንደእነ ናቡከደነፆር፣ ከቂሮስና ከሜዶናዊው ዳርዮስ ጋር የሠራ ጥበበኛ አገልጋይ ነው፡፡ በተጨማሪም ዳንኤል ታማኝና ቅን አገልጋይ፣ እምነተ ጠንካራ፣ ነቢይነት ከአስተዳዳሪነት ጋር የተካነ ወጣት ነበር(ዳን 1፡3)፡፡ ዳንኤል የከለዳውያን ቋንቋና ባህል ተምሮ በንጉሡ ቤት እንደተሾመ ከመጽሐፉ እንረዳለን(ዳን 1፡3-21)፡፡ ዳንኤል የሚለው ስም በነቢዩ ሕዝቅኤል ውስጥ ከኖኅና ከኢዮብ ጋር ሁለት ጊዜ ተደጋግሞ ስለተጠቀሰ ትንቢተ ሕዝቅኤልን ያነበቡ ዳንኤል ጻድቅ እንደነበር በቀላሉ ይገነዘባሉ (ሕዝ 14፡12-23)፡፡ የመጽሐፉ ዋና ገጸ ባሕርይ የሆነው ዳንኤል ግን በ605 በምርኮ ወደ ባቢሎን የተወሰደ በመሆኑ የኖረው ከ620 ዓ.ዓ እስከ 539 ዓ.ዓ ድረስ እንደሆነና ባቢሎን ውስጥ ሞቶ እንደተቀበረ ይገመታል፡፡ ዳንኤል ባቢሎን ውስጥ በስደት በሚኖርበት ጊዜ አብረውት የተሰደዱ ሦስት ወዳጆች እንደነበሩት ይታወቃል፡፡ በስደት በነበሩበት ጊዜ የዳንኤል ሦስቱ ወዳጆችም በተመሳሳይ መልኩ ስማቸው ተቀየረ፡፡ በዚህም መሠረት ዳንኤል ብልጣሶር፣ ሐናንያ ሲድራቅ፣ ሚሳኤል ሚሳቅ፣ ዐዛርያን አብደናጎ ተብለው ተጠሩ (ዳን 1፡7)፡፡ አብደናጎ የሚለውን ስም ላይ የመጨረሻው ክፍል "ናጎ" ባቢሎናውያን ከሚያመልኩአቸው አማልክት ውስጥ የአንዱ ስም ሲሆን "ሚሳቅ" የሚለው ደግሞ ሌላ "ሚሳቅ" የሚባል የባቢሎናውያን አማልክት ስም መሆኑን ይታወቃል፡፡ በአጠቃላይ በባቢሎናውያን ንጉሥ ባለሟሎች አለቃ አማካይነት የተቀየሩት ስሞች ከባቢሎናውያን አማልክቶች ጋር የተቆራኘ ትርጓሜ ያላቸው ናቸው፡፡ የተጻፈበት ዘመን፣ ሥፍራና ይዘት መጽሐፉ የሚሸፍነው ረዥም ታሪክ ወይም ብዙ ዘመናት ውስጥ የተከናወኑ ድርጊቶችና በተለያዩ ጊዜያት ስለተነሡት ኃያላን ነገሥታት ስለሆነ በአንድ ጊዜና በአንድ ሰው የተጻፈ ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡ መጽሐፉ በብዙ ሊቃውንት ዘንድ ከክርስቶስ ልደት በፊት በስድስተኛው መቶኛ ክፍለ ከመን ሊጻፍ እንደሚችል ቢያምኑም ሌሎች ግን ይህንን በመቃወም ከክርስቶስ ልደት በፊት በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ተጽፏል እንደሚሉት ሊቃውንት አገላለጽ፤ ትንቢተ ዳንኤል የተጻፈው እንዲያውም አንጥዮኩስ ኤጲፋኑስ አራተኛው የተባለው መሪ የግሪክን ሥልጣኔ በአይሁዳውያን ዘንድ የማስፋፋት ዘመቻውን ባጠናከረበት ወቅት እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ አንጥዮኩስ ኤጲፋኑስ አራተኛው ቤተ መቅደስን በማርከስና የአይሁድን ሃይማኖት በመቃወም ከፍተኛ ዘመቻ ያደረገው ከ168 እስከ 164 ዓ.ዓ ባለው ጊዜ እንደሆነ ከጽሑፉ ይዘትና ከታሪክ መዛግብት ያረጋግጣሉ፡፡ ሆኖም በክርስትና በአዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ ትንቢተ ዳንኤልን ሲጠቅስ (ማቴ 24:15)፣ የተነበየው ማርከስ ገና ወደፊት በዚህ ዓለም ወደ መጨረሻው ቀን እንደሚደርስ ዳግመኛ አረጋገጠ፤ ስለዚህ ብዙዎች ትንቢቱ ስለ አፊፋኖስ አይሆንም በማለት ያምናሉ። ዕብራይስጡ መጻሕፍት ከነአዋልድ መጻሕፍትና ተረፈ ዳንኤል ጭምር በ፸ ሊቃውንት ወደ ግሪክኛ ቋንቋ መተረጎሙ የተጀመረው ከአፊፋኖስ ዘመን አስቀድሞ ከ250 ዓክልበ. አካባቢ ጀምሮ ስለ ነበር፣ በአፊፋኖስ ዘመን ተጻፈ ለማለት ልዩ መግለጫዎች ይፈልጋል። እንዲሁም በታላቁ እስክንድር ዘመን (340 ዓክልበ ያሕል) የኢየሩሳሌም ቄሳውንት ከትንቢተ ዳንኤል ስለ ጠቀሱ እስክንድር ከተማቸውን አልፈረሰም የሚል ታሪክ በፍላቪዩስ ዮሴፉስ (100 ዓም ግድም) ጽሑፍ ውስጥ ይገኛል። ትንቢተ ዳንኤል በዕብራይስጥና በአራማይስጥ ቋንቋዎች የተጻፈ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ በዕብራይስጥ ይጀምርና በምዕራፍ 2፡4 ላይ ወደ አራማይስጥ ቋንቋ ይቀየራል፤ በድጋሚ በምዕራፍ 8፡1 ላይ ወደ ዕብራይስጥ ቋንቋ ተመልሶ እስከ መጨረሻው በዚሁ ቋንቋ ይደመድማል፡፡ በእርግጥ አራማይስጥ በስደት የቆዩበት ቦታ ቋንቋ መሆኑ ሲነገር ዕብራይስጥ ደግሞ የስደተኞቹ የእስራኤላውያን ቋንቋ ነበር፡፡ ጸሐፊው በዕብራይስጥ መጻፍ ከጀመረ በኋላ በስደት ጊዜ የተወለዱ ብዙ እስራኤላውያን ከዕብራይስጥ ይልቅ የተሰደዱበት ቦታ ቋንቋ የሆነውን አራማይስጥ መረዳታቸው በመገንዘቡ ምክንያት ወጣት ስደተኞችንም ለመርዳት በማሰብ ጭምር በአራማይስጥ መጻፍ ጀመረ የሚል መላ ምት በአንዳንድ ሊቃውንት ቀርቧል፡፡ ከ40 ዓም እና 90 ዓም መካከል ጽሑፉ እጅግ እንደ ተለወጠ ሊታወቅ ይቻላል። ምክንያቱም ከዚያ አስቀድሞ የነበሩት ግሪክኛ (፸ ሊቃውንት) እና ከቁምራን ጥቅል ብራናዎች መካከል የተገኘው ዕብራይስጥ /አራማይስጥ ትርጉም ከለውጦቹ በፊት የነበረው አጻጻፍ ያሳያሉ። በ90 ዓም ግን በተለይ በአይሁዶች ረቢው አኪቫ በን ዮሴፍ ጥረት፣ የብሉይ ኪዳን ቃላት በመላው ተቀየሩ፤ በተለይም ትንቢተ ዳንኤል በዚያም ውስጥ በተለይ ምዕራፍ 11 እጅግ ተቀየሩ። በትንቢተ ዳንኤል ውስጥ ለውጦቹ ከግሪኩ በተለይ ስለ በዙ፣ በ140 ዓም ያሕል ጤዎዶትዮን የተባለ አንድ አይሁዳዊ መምኅር አዲስ ግሪክኛ ትርጉም ሠራ፤ ይህም ከአኪቫ ማሶራዊ ትርጉም ጋር ይስማማል። ዛሬውም በእንግሊዝኛም ሆነ በአብዛኞቹ ልሳናት የትንቢተ ዳንኤል ትርጉም የአኪቫን ማሶራዊ ዕብራይስጥ ትርጉም ይከተላል፤ ነገር ግን በመጀመርያ ክፍለ ዘመናት የኖሩት ክርስትያኖች ከጤዎዶትዮን በፊት የተገኘውን «ጥንታዊ ግሪክ ዳንኤል» ያንብቡ ነበር። የመጽሐፉ ይዘት፣ ያጻጻፉ ስልት መለያየት፣ የተጻፈበት ቋንቋ ከአንድ በላይ መሆን፣ ያካተታቸው ታሪኮች ይዘት፣ የሕልሞችና ራእዮች ሁኔታ እንዲሁም የተጠቀመው የዘመን አቆጣጠር ሲታይ በአንድ ጸሐፊና በአንድ ወቅት የተጻፈ ነው ብሎ ለማመን ያስቸግራል፡፡ ምናልባት የታሪኩ ዋናው ክፍል ቀድሞ ተጽፎ በኋላ ሌሎች የቀድሞውን ጽሑፍ በመከለስ አዳዲስ ነገሮችን አካተው በድጋሚ ጽፈውት ሊሆን እንደሚችል ይታመናል፡፡ የመጽሐፉ ይዘት በምናይበት ጊዜ ሕልምና ራእይ፣ በደግና በክፉ መካከል የሚደረጉ ትግሎች፣ ምሳሌያዊ ቁጥሮች፣ ስለ ዓለም መጨረሻ ክንውኖች፣ የፍርድ ሂደቶች ከታሪካዊ ክስተቶች ጋር አጣምሮ የያዘ ነው፡፡ መጽሐፉ የጻፈው ወይንም የጻፉት ሰዎች ቅዱሳት መጻሕፍትን ያወቁና ያገናዘቡ እንደሆኑ ጽሑፉ ውስጥ ከተካተቱት ከቀድሞ የነቢያቶች፣ የጥበብና የኦሪት መጻሕፍት ጥቅሶች መረዳት ይቻላል፡፡ በአጠቃላይ በመጽሐፉ የመጀመሪያው ክፍል ውስጥ ልብ ሰቃይ የሆኑ የፍርድ ሂደቶችና እምነትን በመፈታተን ወደ ክህደት ሊመሩ የሚችሉ ክንውኖች ቢኖሩም የመጽሐፉ ዋና ገጸ ባሕርይ የሆኑት ዳንኤልና ሦስቱ ወዳጆቹ ግን በእግዚአብሔር ላይ ባላቸው የእምነታቸው ጽናት አሸናፊዎች ሆነው በመወጣት ነገሩን በድል ሲያጠናቅቁ ይታያል፡፡ የመጽሐፉ ሁለተኛው ክፍል ግን(ዳን 7-14) አብዛኛው ትኩረቱ ዳንኤል በሚያያቸው ራእዮችና መላእክቶች በሚሰጡት የራእዮቹ ትርጓሜ ላይ ነው፡፡ ዳንኤልና ሦስቱ ወዳጆቹ በስደት ወደ ባቢሎን ተማርከው ታዋቂና የንጉሥ አገልጋይ ሆኑ በወቅቱ የባቢሎን ንጉሥ የነበረው ናቡከደነፆር አይሁዳውያን ብልኾችና ጠንካሮች እንደሆኑ ያውቅ ስለነበር በቤተ መንግሥቱ ውስጥ የሚያገለግሉት አይሁዳውያን ተመርጠው እንዲዘጋጁ አዘዘ፡፡ በዚህም መሠረት ዳንኤልና ሦስቱ ወዳጆቹ በባቢሎን ውስጥ እያሉ ከእስራኤል ምርኮኞች መካከል ተመርጠው ለሦስት ዓመት ከሠለጠኑ በኋላ በንጉሡ ፊት ቀርበው ሥራቸውን እንዲ ምሩ ተወሰነ(ዳን 1)፡፡ዳንኤልም ደስ የሚያሰኘው የንጉሡን ምግብ በመመገብና የወይን ጠጁንም በመጠጣት ራሱን ላለማርከስ ቁርጥ ውሳኔ በማድረግ የአትክልት ምግብ ብቻ ይመገብ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ለዳንኤልና ለሦስቱ ወዳጆቹ በማናቸውም ጥበብና ሥነ ጽሑፍ ዕውቀትና ማስተዋል ሰጣቸው፤ ዳንኤል ግን በተጨማሪ ራእይንና ሕልምን የመተርጐም ችሎታ ነበረው፡፡ በናቡከደነፆር ፊት ቀርበው ማገልገል ሲጀምሩም በማናቸውም ጥበብና ማስተዋል ንጉሡ ለሚያቀርበው ጥያቄና እንቆቅልሽ ሁሉ ፈጥኖ መልስ በመስጠት ረገድ በግዛቱ ካሉት ጠንቋዮችና አስማተኞች መካከል እነርሱ ዐሥር ጊዜ ብልጫ ያላቸው ሆነው ተገኙ፡፡ በዚህ ሁኔታ መጽሐፉ ገና ከጅምሩ ዳንኤልን በድሎትና በሥልጣን የማይበገር ጥበበኛ፣ ታማኝና የወገኖቹን ባህልና ሥርዓት ጠባቂ አድርጎ ያቀረበዋል፡፡ ይህ መሆኑ ለቀጣዩ ክፍል እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ በእርግጥ በቀጣዩ ክፍል ይህንን ጥበቡና ታማኝነቱ ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያደረሱትና ዝናውን የበለጠ የገነነ እንደሚያረጉት ያስገነዝባል፡፡ ቀጥሎም ዳንኤል ለንጉሥ ናቡከደነፆር የናቡከደነጾር የምስል ሕልምን ከነትርጓሜው ገለጠለት(ዳን 2)፡፡ ይህ ጥበብ የተሞላበት ድርጊቱ በንጉሡ ታላቅ የክብር ቦታ እንዲቀመጥ፣ ብዙ ስጦታዎች እንዲያገኝ፣ በባቢሎን ግዛቶችም ሁሉ ላይ የበላይ ገዥ እንዲሆንና በባቢሎንም ጠቢባን ሁሉ ላይ አለቃ እንዲሆን አደረገው፡፡ ከዚህ በኋላ ለዳንኤል ሦስቱ ወዳጆች የመጀመሪያው የመፈተኛ ጊዜ ይሆናል(ዳን 3)፡፡ በዚህ አስቸጋሪ የፈተና ጊዜ ሦስቱ የዳንኤል ጓደኞች ለወርቁ ምስል ባለመስገዳቸው ተከሰሱ፤ በሞት እንዲቀጡ ተፈረደባቸው፤ በመጨረሻ ግን በእምነታቸው ጽናት ምክንያት ታሪኩ ሙሉ በሙሉ ተቀይሮ ከእሳት ውስጥ ወጥተው ተሾሙ፡፡ ዳንኤል ሁለተኛውን የናቡከደነፆር ሕልም እንደ ተረጐመ፤ ናቡከደነፆርም ለእግዚአብሔር ምስጋና አቀረበ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ሁኔታ እግዚአብሔር በሰጠው ብልኀት፣ዕውቀትና፣ ጥበብ በመመራት ዳንኤል ንጉሥ ቤልሻጻር ያየውን ምሥጢራዊ ጽሑፍ ነገር ግን ማናቸውም ጠቢባን አማካሪዎቹና አስማተኞቹ ሁሉ ሊተረጉሙት ያልቻሉትን ለንጉሡ ገለጠ፡፡ በዚህም ምክንያት የክብር ምልክት የሆነውን የወርቅ ሐብል በአንገቱ እንዲያደርጉለትና በመንግሥቱም ሥልጣን ሦስተኛውን ማዕረግ እንዲይዝ በዐዋጅ ተነገረ(ዳን 5)፡፡ በዚህ ምክንያት ዳንኤልና ሦስቱ ወዳጆቹ ባቢሎን(የዛሬዪቱ ኢራቅ) ውስጥ ትልቅ የክብር ቦታ ተቀዳጁ፡፡ የዳንኤልና ሦስቱ ወዳጆቹ ታማኝነታቸው ምስክር በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ ታማኝነት የመጽሐፉ ዋና ትኩረት ስለሆነ ይህንን ታማኝነት ግልጽ በሆነና ትምህርት ሰጭ በሆነ መልኩ ተደጋግሞ ተገልጿል፡፡ ዳንኤልና ሦስቱ ወዳጆቹ ለእግዚአብሔርና ላደጉበት አይሁዳዊ ባህልና ሥርዓትፍጹም ታማኝ መሆናቸውን በተለያየ መልኩ ተገልጿል፡፡ ዳንኤልና ወዳጆቹ በንጉሡ ቤት በልዩ ሁኔታ የተዘጋ ምግብና ወይን ጠጅ እየተመገቡና እየጠጡ እንዲያገለግሉ ቢፈቀድላቸውም መቀበል አልፈለጉም፡፡ የንጉሡን ምግብ በመመገብና የወይን ጠጁንም በመጠጣት ራሳቸውን ላለማርከስና አትክልት ብቻ እየተመገቡና ውሃ እየጠጡ ለመቆየት መምረጣቸውን ነው(ዳን 1፡8)፡፡ በእርግጥ በኦሪት ዘሌዋውያን ምዕራፍ 11 ላይ እግዚአብሔር ለሙሴና ለአሮን ለምግብነት መዋል ስለሚገባቸውና ስለሌለባቸው ወይም ስለ ረከሱ እንስሳትና አዕዋፋት በተመለከተ የአመጋገብ ሥርዓት ሲሰጥ ይታያል፡፡ ባቢሎናውያን ምንአልባት ከእነዚህ ከተከለከሉት እንስሳትና አዕዋፋት መካከል ውስጥ ይመገቡ ነበር፡፡ ዳንኤልና ወዳጆቹ ግን ለአይሁዳዊነት ባህልና ሥርዓት እንዲሁም ለእግዚአብሔር ሕግ ታማኝነታቸውና ታዛዥነታቸው የንጉሡን ምግብ ላለመብላት በመወሰን አሳይተዋል፡፡ ቀጥሎም ለእግዚአብሔር ታማኝነት የተገለጸው በሦስቱ የዳንኤል ወዳጆች ሲሆን ይህም ናቡከደነፆር ላቆመው የወርቅ ምስል አንሰግድም በማለታቸው ምክንያት በሚነደው የእሳት ነበልባል ውስጥ እስከመጣል መድረሳቸውን ነው፡፡ እነዚህ ሦስቱ የዳንኤል ወዳጆችም እኛ የምናገለግለው አምላክ ከዚህ ከሚነድደው ከእሳቱ ነበልባልም ሆነ ከአንተ እጅ ሊያድነን ይችላል፤ ንጉሥ ሆይ! እርሱ ሊያድነን ፈቃዱ ባይሆን እንኳ አማልክትህን እንደማናመልክና ላቆምኸው የወርቅ ምስል እንደማንሰግድ ዕወቅ በማለት ቈራጥነታቸውንና ታማኝነታቸውን ለእግዚአብሔር ገለጹ(ዳን 3፡17-18)፡፡ ታማኝነታቸውና ከእግዚአብሔር የተደረገላቸውን ጥበቃ ንጉሡን ጭምር ያስደነቀ እንደነበር ሲገልጽ አስረን በሚነደው የእሳት ነበልባል ውስጥ የጣልናቸው ሰዎች ሦስት ብቻ አልነበሩምን? እነሆ እኔ እሳቱ ምንም ሳይጐዳቸው ከእስራት ተፈትተው በነበልባሉ ውስጥ የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ አራተኛውም የአማልክትን ልጅ ይመስላል ይላል(ዳን 3፡24-25)፡፡ቀጥሎ የምናገኘው የዳንኤል መፈተንና ያሳየውን ግንነት የተሞላበት ታማኝነቱን ነው፡፡ የንጉሥ ዳርዮስ መሳፍንት ወደ ንጉሡ በመሄድ ዳንኤል አንተን አያከብርህም፤ ፈርመህበት የወጣውንም ዐዋጅ በመጣስ በቀን ሦስት ጊዜ ወደ አምላኩ ይጸልያል ብለው በመክሰስና ንጉሥ ያስተላለፈው ዐዋጅ ወይም ትእዛዝ መለወጥ እንደማይቻል ለንጉሡ በማረጋገጥ በአንበሶች ጉድጓድ እንዲጣል አደረጉት(ዳን 6፡15-16)፡፡ ይህ ከመደረጉ በፊት ግን በድርጊቱ እጅግ በጣም ያዘነው ንጉሥ ዳርዮስ ዳንኤልን ሁልጊዜ በታማኝነት የምታገለግለው አምላክህ ያድንህ በማለት አበረታታው(ዳን 6፡16)፡፡ የታመኑትን ሁሌም የሚታደገው አምላክ ዳንኤልን በአንበሶች እንዲቦጫጨቅ አልፈቀደምና አንበሶቹ እንዳይጎዱኝ እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ አፋቸውን ዘጋ፤ ይህንንም ያደረገው እኔ ንጹሕ መሆኔንና አንተንም አለመበደሌን ስላወቀ ነው በማለት በውሳኔው ተረብሾ እንቅልፍ አጥቶ ላደረው ለንጉሡ ይገልጽለታል(ዳን 6፡21)፡፡ በዳንኤል ምስክርነትና ባዳነው አምላክ የተደነቀው ንጉሥ ዳርዮስ በመንግሥቴ የሚኖር ሕዝብ ሁሉ የዳንኤልን አምላክ እንዲፈራና እንዲያከብር በዐዋጅ አዝዣለሁ፤ እርሱ ሕያውና ዘላለማዊ አምላክ ነው፤ እርሱ ዘላለማዊ ንጉሡ ነው፤ ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም በማለት ለሕዝቡ ትእዛዝ አስተላለፈ(ዳን 6፡ 26-27)፡፡ በአጠቃላይ በዳንኤልና በሦስቱ ወዳጆቹ የተከናወኑት ግንነት የተሞላባቸው ምስክርነቶች አይሁዳውያን ሃይማኖታቸው፣ ባህላቸው፣ ሥርዓቶቻቸው ጠብቀው ለእግዚአብሔር ታማኝ ሆነው ለማንኛውም አረማዊ ንጉሥ ሳይፈሩ፣ ሳይንበረከኩና በጥቅማጥቅምና በሥጋዊ ድሎት ሳይታለሉ መመስከርና በእምነታቸው መጽናት እንዳለባቸው የሚያሳይ ነው፡፡ ስለ ሙታን መነሣትና ስለ መጨረሻው ፍርድ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከሞት በኋላ ስላለው ፍርድና የሕይወት ሁኔታ የሚገልጹ የመጽሐፍ ክፍሎች እጅግ በጣም ጥቂት ናቸው፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ትንቢተ ዳንኤል ከሞት በኋላ ስለሚኖረው ፍርድና የእያንዳንዱ ሰው የመጨረሻ እጣ ፈንታ ምንም በማያሻማ ሁኔታ ስለሚገልጽ ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት እንደ ዋና መረጃ ሆኖ ይጠቀሳል፡፡ትንቢተ ዳንኤል አገላለጽ ዳግመኛ ሕይወት ወይም ትንሣኤ በምንልበት ጊዜ ከሞት በኋላ በነፍስ ብቻ ሳይሆን በሥጋና በነፍስ ሕይወት ማግኘትን ያመለክታል፡፡ በእርግጥ አንዳንድ መጻሕፍት ሰዎች ሥጋቸው በስብሶ መሬት ውስጥ እንደማይቀር፣ በሥጋ እንደሚነሡና ዘላለማዊ ሕይወት አግኝተው እንደሚኖሩ ያስገነዝባሉ(መዝ16፡9-11፤ ኢሳ 26፡19)፡፡ እንደ ትንቢተ ዳንኤል አገላለጽ የዓለም ፍጻሜ ከመሆኑ በፊት ሕዝቡን ሁሉ የሚፈታተንና ለሥቃይ የሚዳርግ በምድር ላይ ታላቅ የመከራ ጊዜ ይመጣል(ዳን 12፡1)፡፡ በምድር ላይ ምንም እንኳ አስቸጋሪ የሆነ የመከራ ጊዜ ቢከሰትም ስማቸው በእግዚአብሔር መጽሐፍ የተጻፉት ግን ይድናሉ(ዳን 12፡1)፡፡ እነዚህ በታማኝነት ጸንተው በመኖር የመከራ ጊዜን በብቃት የሚወጡትና ስማቸው በእግዚአብሔር መጽሐፍ የተጻፉት በፈተና ነጥረውና ጠርተው በመውጣታቸው እንከን የሌለባቸው ስለሚሆኑ ቢሞቱም ተነሥተው በመጨረሻው ቀን የክብር ድርሻቸውን እንደሚያገኙ መልአኩ ለዳንኤል ያረጋግጥለታል(ዳን 11፡35፤12፡ 10-13)፡፡ ስለዚህ አስቀድመው በሞት ተለይተው የነበሩት ተነሥተው እንደገና በሕይወት ይኖራሉ፤ ከእነርሱም እኩሌቶቹ የዘላለም ሕይወት አግኝተው ሲደሰቱ እኩሌቶቹ ለዘላለም በሐፍረትና በጉስቁልና ይሠቃያሉ(ዳን 12፡2)፡፡ የዘላለም ሕይወት አግኝተው ከሚደሰቱትም መካከል ውስጥ ጠቢባኖችና ብዙ ሰዎችን በማስተማርና ጥበባቸውን አገልግሎት ላይ በማዋል ሌሎችን ከክፉ መንገድ ወይም ከጥፋት ጐዳና ወደ ደግ ሥራ የመለሱ ሁሉ ብልጫ እንዳላቸው ይገልጻል(ዳን 12፡3 እና 10)፡፡ መላእክትና አገልግሎታቸው መላእክት ተላላኪ መልእክተኞች፣ በፍጥረታቸው ረቂቃን የሆኑ፣ ብዛታቸው የማይቆጠር፣ ኃይላቸው ብርቱ፣ ቅዱሳን ጠባቂዎች፣ ስለ ታናናሾች በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ አልፎ አልፎ ራሳቸውን በሰው መልክ የሚገልጹና እግዚአብሔርንም የሚያመሰግኑ መሆናቸው በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ በተለያየ መልኩ ተጠቅሶ እናገኘዋለን(ዘፍ 19፡1 እና 12፤ ኢዮ 1፡6፤ ዳን 8፡15-26፤ ኢሳ 6፤ ዘካ 14፡5፤ ማቴ 18፡10፤ ማቴ 22፡30፤ ማቴ 24፡36፤ ሉቃ 15፡10፤ ሉቃ 24፡39፤ ራእ 5፡11-12፤ ዕብ 1፡4)፡፡ በትንቢተ ዳንኤል ውስጥ ግን መላእክቶች ግልጽ በሆነ ሁናቴ በስማቸው እየተጠሩ የተለያዩ የአገልግሎት ተግባራት ሲወጡ ይታያል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የመጀመሪያው መላኩ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ መላኩ ገብርኤል ዳንኤል ወደነበረበት ቦታ በመድረስ ግራ የተጋባባቸውና መፍታት ያልቻላቸውን ራእዮች በመተንተን ያስረዳዋል (ዳን 8፡15-27፤ ዳን 9፡21-27)፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ዳንኤል ስለ እስራኤላውያን ኃጢአት እየተናዘዘ ምሕረትን ከእግዚአብሔር ሲለምን መላኩ ገብርኤል ወደ እርሱ በመቅረብ ገና መጸለይ ስትጀምር እግዚአብሔር ልመናህን ሰምቶአል፤ እርሱ ስለወደደህም የጸሎትህን መልስ ልነግርህ መጥቼአለሁ፤ እንግዲህ የራእዩን ትርጉም ስነግርህ በጥንቃቄ አድምጠኝ በማለት የእግዚአብሔር ተላላኪነቱና ራእይ ፈቺነቱ ይገልጻል(ዳን.9፡23)፡፡ በተጨማሪም መላኩ ገብርኤል እኔ ወደዚህ የመጣሁት የትንቢቱን ምስጢር እንድታውቅ ጥበብንና ማስተዋልን ልሰጥህ ነው በማለት ጥበብንና ማስተዋል እንዲሰጥ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላከ መሆኑን ይገልጻል(ዳን 9፡22)፡፡ ከዚህ የምንረዳው መላኩ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ጋር ቀረቤታ እንዳለው፣ ሰዎች ግራ ተጋብተው ችግራቸውን ለእግዚአብሔር በጸሎት በሚገልጹበት ጊዜ የጸሎታቸውን ምላሽ በመያዝ በፍጥነት የሚደርስ፣ ራእዮችን በመፍታት ነገሮች ግልጽ የሚያደርግ ታማኝ መልእክተኛ ነው፡፡ ሌላው በትንቢተ ዳንኤል ውስጥ በስም የተጠቀሰውና ብዙ የአግልግሎት ተግባራት የሚፈጽመው መላኩ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ዳንኤል በጤግሮስ ወንዝ አጠገብ በሐዘን ላይ ለሦስት ሳምንታት ሥጋም ሆነ ሌላ ምግብ ሳይበላ፣ የወይን ጠጅም ሳይጠጣና ቅባትም ሳይቀባ በቆየበት ጊዜ አስደናቂ የሆነ ራእይ አየ (ዳን 10፡2-8)፡፡ በዚህ ጊዜ ዳንኤል ኃይሉ ሁሉ ተሟጦ እጅግ በጣም ከመድከሙ የተነሣ መልኩ ተለዋውጦ ባየው ራእይ በመደንገጥ እንደ በድን ሆኖ መሬት ላይ ወደቀ፤ በፍርሃትም ተንቀጠቀጠ (ዳን 10፡9)፡፡ በዚህ ጊዜ በስም ያልተጠቀሰ መልአክ ወደ ዳንኤል ደርሶ ደጋግፎ በእጁና በእግሩ እንዲቆም ካደረገው በኋላ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተወደድህ ዳንኤል ሆይ! እነሆ እኔ ወደ አንተ ተልኬ መጥቻለሁ፤ ባለህበት ጸጥ ብለህ ቁም፤ የምነግርህም ጸጥ ብለህ አስተውል በማለት ካበረታታው በኋላ የሚነግረውን በጥንቃቄና በማስተዋል እንዲሰማው ያስገነዝበዋል (ዳን.10፡11)፡፡ በመላኩ ንግግር ውስጥ በፋርስ ብቸኛ መሆኔን አይቶ ከመላእክት አለቆች አንዱ የሆነው ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ ካለ በኋላ በድጋሚ በንግግሩ መጨረሻ ላይ የእስራኤል ጠባቂ መልአክ ከሆነው ከሚካኤል በቀር እኔን የሚረዳ የለም በማለት ይደመድማል (ዳን 10፡13 እና 21)፡፡ ከዚህ የምንረዳው መላኩ ሚካኤል የመላእክቶች አለቃ፣ የእግዚአብሔር ሕዝብ ብርቱ ጠባቂ፣ የእግዚአብሔር ታማኞች በብቸኝነት ኑሮ በተጎሳቈሉ ጊዜ ፈጥኖ የሚደርስና የሚረዳ መልእክተኛ እንደሆነ ነው፡፡ በተጨማሪም መላኩ ሚካኤል የዓለም ፍጻሜ በሚሆንበት ጊዜ እንደሚገለጥ ሲናገር ሕዝብህን የሚጠብቀው ታላቁ መልአክ ሚካኤል በዚያን ጊዜ ይገለጣል ይላል (ዳን 12፡1)፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ተጠቅሶ ከአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ውስጥ ትንቢተ ዳንኤልን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በሰፊው የጠቀሰው ዮሐንስ ሲሆን ይህም በራእይ ውስጥ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ "አንድ አውሬ ከባሕር ሲወጣ አየሁ" በማለት ስለ አውሬው የሚዘረዝረውን ዳንኤል 7 ላይ ከተገለጸው አውሬ ጋር እጅግ በጣም ተቀራራቢ የሆነ ተመሳሳይነት አለው(ራእ 13)፡፡ በዮሐንስ ራእይ እንደ መለኮታዊ ተዋጊ፣ ትክክለኛ ፈራጅ፣ ዐይኖቹ በእሳት ነበልባል የተመሰሉት፣ በደም የተነከረ ልብስ የለበሰው፣ ስሙም "የእግዚአብሔር ቃል" ተብሎ የተጠራውና ክፋትን ሁሉ ድል ያደረገው በነጭ ፈረስ ላይ የተቀመጠ ፈረሰኛ ተጠቅሷል፡፡ በትንቢተ ዳንኤል ደግሞ "የሰውን ልጅ የሚመስል በሰማይ ደመና ተከብቦ ሲመጣ አየሁ" ይላል፡፡ እነዚህ ሁለቱ ገጸ ባሕርያት ተመሳሳይነትና ተዛማጅነት እንዳላቸው መረዳት አያዳግትም(ራእ 19፡ 11-21፤ ዳን 7፡ 13)፡፡ በተጨማሪም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተደጋጋሚ ራሱን "የሰው ልጅ" ብሎ ይጠራ እንደነበርና ይህም የሰው ልጅ የሚለው ቃል በትንቢተ ዳንኤል ውስጥ ቀድሞውኑ ተገልጾ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በአጠቃላይ የዮሐንስ ራእይ በብዙ መልኩ ከትንቢተ ዳንኤል ጋር ተመሳሳይነት ስላለው ሳቦቹም ከዛው ጋር የተወራረሱ ስለሆኑ ጸሐፊው ትንቢተ ዳንኤልን እንዳነበበውና የሚጽፈውም ሁሉ በቂ የሆነ የትንቢተ ዳንኤል ተወራራሽ ሳባች እንደተጠቀመ መረዳት ይቻላል፡፡ የእግዚአብሔር መንግሥት ከዓለም መንግሥታት ጋር ሲወዳደር ትንቢተ ዳንኤል እነዚህ ኃያላን መንግሥታት በመጥቀስና ከእግዚአብሔር መንግሥት ጋር በማወዳደር ኃያሉና እውነተኛው መንግሥት የትኛው እንደሆነ አንባቢው እንዲረዳና የራሱን ድምዳሜ ላይ እንዲደርስ ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ ለዳንኤል የተገለጠለት ስለ አራቱ አውሬዎችና ለዘላለም ሕያው ሆኖ ስለሚኖረው ራእይ ይህንኑ የዓለም መንግሥታትና የእግዚአብሔር መንግሥት የማወዳደር ሁኔታ ይንጸባረቃል (ዳን 7)፡፡ በዚህ ራእይ እንደምንረዳው ከአራቱ ማእዘናት የተነሣውነፋስ ታላቁን ባሕር ባናወጠው ጊዜ አራት የተለያዩ ታላላቅ አውሬዎች ከባሕሩ ወጡ። እነዚህም በአንበሳ፣ በድብ፣ በነብርና አንድ ኃይለኛ፣ አስቀያሚና አስፈሪ በሆነ እንስሳቶች የተመሰሉ ነበሩ። ይችም አንበሣ የንሥር ክንፎች የነበራትና የንሥር ክንፎቿም የሚነቀሉባት አውሬ ናት። አራተኛዋም አስቀያሚዋ አውሬ ፲ ቀንዶች (አለቆች) አሏት፤ ከነዚህም መካከል ሌላ ትንሽ ቀንድ ለትወሰነ ጊዜ በትዕቢት እየተናገረ ዓለሙን ይጨቆናል። ከትግሎች ሁሉ በኋላ በመጨረሻም እነዚህ አውሬዎች ሥልጣናቸውን ተነጠቁ። በሌላ መልኩ የሰውን ልጅ የሚመስል በሰማይ ደመና ተከብቦ ሲመጣ ታየ፡፡ ይህ በሰው ልጅ የተመሰለው ግን ለዘላለም ሕያው ወደሆነው ፊት አቀረቡት፡፡ በልዩ ልዩ አገር የሚኖሩ ሕዝቦችና ልዩ ልዩ ቋንቋ የሚናገሩ ነገዶች ያገለግሉት ዘንድ ሥልጣን፣ ክብርና ኀይል ተሰጠው፤ ሥልጣኑ ለዘላለማዊ ነው፤ ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም(ዳን 7፡1-14)፡፡ በምዕራፍ 8 ስለ «ፍጻሜ ዘመን» የሆነ ሌላ ራዕይ ይታያል። ይህ የአውራ በግና አውራ ፍየል ትርዒት ነው። ፍየሉ በምድር ስፋት ሁሉ ምድርን ሳይነካ አውራ በግ በኤላም መታ፣ ፪ ቀንዶቹን ሰበረ። መልዓኩ እንደሚያስረዳው የበጉ ፪ ቀንዶች መታወቂያ የማዴ (ሜዶን)ና የፋርስ ነገሥታት ሲሆኑ፣ የፍየሉም መታወቂያ የያዋን (ግሪክ ወይም ምዕራባውያን) ንጉሥ ነው። ከዚህ ትግል በኋላ፣ ፍየሉ ይታበያል፣ አንድያ ቀንዱ ተነቅሎ አራት ቀንዶች ይከተላሉ፤ ከነዚህም አራት ቀንዶች መካከል ትንሽ ቀንድ ይነሣል፤ ትንሹም ቀንድ እንደ ምዕራፍ 7 ለተወሰነ ጊዜ ዓለሙን በጭካኔ የሚገዛው ነው። በመጨረሻም ከዳን 10-11 እንደምንረዳው ሌሎችም ታላላቅ «የስሜን» ነገሥታት የተባሉትም ተነሥተው ለጥቂት ጊዜያት ከገዙ በኋላ ይወድቃሉ። ታላላቅ ከተባሉትም ውስጥ መጨረሻው ክፉ ንጉሥ የኤዶም፣ ሞአብና አሞን፤ የግብጽ፣ የሊቢያና የኢትዮጵያ ሀብቶች ወይንም ሰዎች ይበዝብዛል (ዳን 11፡43)። (በዕብራይስጥ ትርጉም፣ እነዚህ መጨረሻ ሦስቱ የካም ልጆች ምጽራይም፣ ፉጥና ኩሽ ስሞች ናቸው። በአራተኛው ልጅ በከነዓን ፈንታ ግን የአብርሃም ዘሮች የነበሩት «ኤዶም፣ ሞአብና አሞን» አለው።) ይህ ስስታም ንጉሥ በመጨረሻው ይጠፋል፤ የሚረዳውም አይገኝም (ዳን 11፡45)። ከተወሰኑት ቀኖች ቁጥር በኋላ ግን፣ የእግዚአብሔር መንግሥትና በታማኝነት የሚኖሩት ሕዝቦቹ ጸንተው ይኖራሉ። ቢሞቱም እንኳ በመጨረሻው ቀን በሙታን ትንሳኤ የክብር ድርሻቸውን ያገኛሉ (ዳን 12)። ሌላው በዳንኤል ከተተረጐመው የመጀመሪያው የንጉሥ ናቡከደነፆር ሕልም (ዳን 2) እንደምንረዳው በዓለም ላይ ኃያላን የተባሉና በወርቅ፣ በብር፣ በነሐስና በብረት የተመሰሉ አራት መንግሥታት ይነሣሉ። መጀመርያውም ባቢሎን መሆኑን ሲነገር፣ በተለመደው የተረፉት ፋርስ፣ ግሪክ እና የሮሜ መንግሥት ትንቢት እንደ ነበሩ ይታመናል። የእነዚህም ሕልሞች ፍቺ እንደሚያስረዱት ለናቡከደነፆር የሰማይ አምላክ መንግሥትንና ኃይልን፣ ሥልጣንና ክብርን እንደሰጠውና በሕልሙ ያየውን የወርቁ ራስ እንደሆነ ዳንኤል ያረጋግጥለታል (ዳን 2፡38)። ቀጥሎም ሌሎች ሦስት መንግሥታት እንደሚነሡ ከገለጸ በኋላ በነሐስና በብረት የተመሰሉት ሦስተኛውና አራተኛውን እጅግ በጣም ኃያላን ዓለምን ለመግዛትና ሁሉንም ነገር ለመሰባበርና ለማንኮታኮት የሚችሉ እንደሚሆኑ ያስገነዝባል። ነገር ግን በእነዚያም ነገሥታት ዘመን የሰማይ አምላክ ፈጽሞ የማይፈርስና ግዛቱም በሌላ ሕዝብ የማይደፈር መንግሥትን ይመሠርታል፤ ይህ መንግሥት ሌሎችን መንግሥታት እስከ መጨረሻው ያጠፋቸዋል፤ እርሱ ግን ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል ። መጽሐፍ ቅዱስ
9987
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%85%E1%88%A9%E1%8B%AD%20%E1%8B%88%E1%88%8D%E1%8B%B0%E1%88%A5%E1%88%8B%E1%88%B4%20%28%E1%89%A5%E1%88%8B%E1%89%B4%E1%8A%95%20%E1%8C%8C%E1%89%B3%29
ኅሩይ ወልደሥላሴ (ብላቴን ጌታ)
ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ በኢትዮጵያ መኻል አገር በሰሜን ሸዋ በመርሐ ቤቴ አውራጃ በታች ቤት ወረዳ ረመሸት ቀበሌ ደን አቦ ገዳም በተባለ ሥፍራ በ ፲፰፻፸፩ ዓ.ም ተወለዱ። ሲወለዱ የተሰጣቸው ስም ገብረመስቀል ነበር። በቤተ ክህነት ትምህርት እንጦጦ ራጉኤል ደብር መጥተው የመጻሕፍትን ትርጓሜ በዘመኑ ከነበሩት የደብሩ ሊቃውንት ዘንድ ተምረው አጠናቀዋል። እዚህ ነው አንዱ መምህራቸው «አንተ የቀለም ቀንድ ስለሆንክና በምግባርህም የተመሰገንህ ነህና፡ ኅሩይ የተባለውን ስሜን ሸልሜያሃለሁ፡ ከንግዲህ ኅሩይ እየተባልክ ተጠራ!» አሏቸው። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ ሃያ አንድ መጻሕፍትን የደረሱ ሲሆኑ፤ የመጨረሻው መጽሐፋቸው «የኢትዮጵያ ታሪክ፡ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል» ለመጀመሪያ ጊዜ በ ፲፱፻፺፱ ዓ.ም የልጅ ልጃቸው ወይዘሮ ሠናይት ተክለማርያም አሳተሙት። የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር እና የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በመተባበር ጳጉሜ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ የተመረቁትን እና ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ እንዲሁም የደራስያን፤- ቀኝ-ጌታ ዮፍታሄ ንጉሤን፤ ነጋድራስአፈወርቅ ገብረ ኢየሱስ፣ እና አቶ ተመስገን ገብሬን ምስል የተቀረጸባቸውን አራት ቴምብሮችን ገበያ ላይ አውለዋል። ደራሲው ፋሽሽት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጋር አብረው ወደ እንግሊዝ አገር ስደት ላይ እንዳሉ በስልሳ ዓመታቸው መስከረም ፱ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. አረፉ። ሥርዓተ ቀብራቸው መስከረም ፲ ቀን እዚያው እንግሊዝ አገር ሲፈጸም ንጉሠ ነገሥቱ የሚከተለውን ንግግር አደረጉ። «አሁን የአዳምን ልጆች ወግ ሲቀበል የምታዩት ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ በአገራችን ሥርዓት በመልካም አያያዝ ያደገ ከኢትዮጵያም ከፍ ካሉት ሊቃውንት የሚቆጠር ነው። ብልሃቱንና ትጋቱንም ለመልካም ሥራ የሚያገለግሉ መሣሪያዎች ስላደረጋቸው በመንግሥታችን ሥራ ለመመረጥና ወደ ታላቁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ለመድረስ በቃ። በየጊዜው የጻፋቸው ከፈትኛ ባህሪውን የሚገልጹ መጻሕፍት፤ ይልቁንም በቤተ ክህነትና በታሪክ እውቀት በዓለም ሊቃውንት ዘንድ የታወቀና የተከበረ አደረጉት። ለምታውቁት ሰው ከታሪኩ ከዚህ የበለጠ ልነግራችሁ የሚያስፈለግ አልመሰለኝም። በአጭሩ ከጠባዩ ትልቅነት የሚሰማኝን ለመናገር ሳስብ ጊዜውን ሁሉ ቁም ነገር በመሥራት ማሳለፉ፤ ከራሱ ይልቅ የተቸገሩትን ለመርዳት መጣሩ፤ እውነትን፣ ፍርድንም ማክበሩና በአገር ፍቅር መቃጠሉ ትዝ ይሉኛል። አገልጋዬና ወዳጄ ኅሩይ! በተቻለህ ስለአገርህ ሥራህን በሚገባ ፈጽመህ በምትሰናበትበት ጊዜ ታላቅ ነህ ሳልልህ ብቀር ሥራዎችህ ቀድመውኝ ይናገራሉ። በክፉ አድራጊዎች የሚገፋ የዓለምን ፀጥታ የሚያናውጥ ነፋስ ምንም ቢያንገላታህና በታላቅ ፈተና ላይ ቢጥልህም ሊያሸንፍ አልቻለም። ታላቅና ቸር በሆነው ጌታ በተመደበው ሕግ ግን መታዘዝ ግድ ሆነብህ። ይህም ለያንዳንዳችን የሚደርሰን ዕድል ነው። አንተም እስከ መጨረሻ ከታገልክ በኋላ ዛሬ ደከመህ፣ አንቀላፋህም። በሥጋ ብትለየንም ስምህና ሥራህ በመካከላችን ይኖራሉ። ኅሩይ! እግዚአብሔር ሲያስበን አጥንቶችህና መንፈስህ የሚሰፍሩበትን ቦታ እስኪያዩና ከአባቶችህ እስኪቀላቀሉ ድረስ በእንግድነት በመጣህበት በዚህ ሥፍራ በሰላም ዕረፍ።» ለልጅ ምክር፣ ለአባት መታሰቢያ-- ለመጀመሪያ ጊዜ 1910ዓ.ም. የታተመ ወዳጄ ልቤ፣ የሰውን ጠባይና ኑሮ በምሳሌ የሚገልጽ -- 1915 ታተመ ስሓርና ወተት፣ የልጆች ማሳደጊያ -- 1922 ታተመ የልብ አሳብ፣ የብርሃኔና የጽዮን ሞገሳ ጋብቻ -- 1923 ታተመ አዲስ አለም፣ የቅኖችና የደግ አድራጊዎች መኖሪያ -- 1925 ታተመ የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች ኅሩይ ወልደሥላሴ
13521
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8D%E1%88%AB%E1%8A%9D%20%E1%8A%A0%E1%88%85%E1%88%98%E1%8B%B5
ግራኝ አህመድ
በተለምዶው ግራኝ አሕመድ ተብሎ የሚታወቀው የጦር መሪ ሙሉ ስሙ ኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሂም አልጋዚ ሲኾን የኖረውም ከ1507 እስክ ታህሳስ 21፣ 1543 (እ.ኤ.አ) ነበር። በዘመኑ በእስልምና ሃይማኖት የኢማምነት ደረጃ የደረሰ ሲኾን የአዳል ግዛት ተብሎ ይታወቅ የነበረውን የጥንቱን የኢትዮጵያ ክፍል በመምራት እንዲሁም በዘመኑ የነበሩትን ነገሥታት ከመካከለኛው የኢትዮጵያ ክፍል እንዲያፈገፍጉ በማድረግ በታሪክ ይታወቃል። በዚህ የተነሳ 3/4ኛ የሚኾነውን የኢትዮጵያ ክፍል ለተወሰነ ጊዜ መቆጣጠር ችሏል። አንድ አንድ የታሪክ ተመራማሪዎችም የግራኝ አሕመድ ሰራዊት ከሞላ ጎደል በሱማሌ ጎሳ ሰዎች የተድሎችን በመቀዳጀቱ ምክኒያት በዚህ ስያሜ እንደጠሩት ይነገራል። ይህ መሪ ከ1529 እስከ 1543 ከነበሩት የመካከለኛው የኢትዮጵያ ክፍል ነገስታት ጋር ጦርነት እንዳረገ ታሪክ ይዘግባል። የኢማም አሕመድ ጎሳ ጻሃፊዎች ዘንድ እንደሚታመነው ግራኝ አረብ እንደነበር ሲሆን በሌሎች ታሪክ ተመራማሪወች ዘንድ ግን ሱማሌ እንደሆነ ነው። እንደ እስራኤላዊው የታሪክ ተመራማሪ ሃጋይ ኽልሪች ግን ግራኝ አህመድ ሱማሊኛ ቋንቋን እንደማይናገር አትቷል። በሌላ ሁኔታ ብዙ የታሪክ ጸሃፍት እና መረጃዎች ግራኝ አህመድ የሐረር ተወላጅ መሆኑን ጠቅሰዋል:: ለግራኝ አህመድ እንቅስቃሴ አስተዋጾ ያደረጉ ነገዶች እንደ ኢሳቅ፣ ዳሩድ እና ማረሃን የተሰኙት የሱማሌ ጎሳወች ሲሆኑ ጎሳወቹ ግን በዘር ምክንያት ሳይሆን ያብሩ የነበሩት በሃይማኖት ተመሳሳይነት ነበር። የኢማሙ ዳግም ድል በኖራ ሀመድ ሁመድ የኢማሙን በ18 ዓመት እድሜ የተገኘ ድል ሰምቶና ደንግጦ መናገሻ ከተማውን ሀረርን ጥሎ ወደ ሶማሊያ የሸሸው ሱልጣን አቡበክር ኪዳር (ኪዳድ) በምትባል ቦታ ተደበቀ። ኢማሙም በነካ እጁ በሙስሊሙ መካከል ፈሳድ እንዲስፋፋና ሙስሊሙ የአንድነት ሀይልና ወኔው እንዲነጥፍ ምክነያት የሆነውን ሱልጣን አቡበክር ለማጥቃት ወደተደበቀበት ከተማ ተጓዘ። ኢማሙ ቦታው ላይ ሲደርሱም ሱልጣኑ ጦሩን አሰልፎ ጠበቃቸው። ሁለቱ ጦሮችም ዝሁር ወቅት ላይ ተገናኙ ኢማሙና ጓዶቻቸውም በኢስላማዊ ህብረትና ሙሐመዳዊ ወኔ ማጥቃት ጀመሩ። በርካታው የሱልጣኑ ሰራዊት ተገደለ። ከፊሉም ሱልጣኑን ጨምሮ ሸሸ። ኢማሙ 20 አመት ሳይሞላቸው ሁለተኛውን ጦርነታቸውን በፍፁም ድል አድራጊነት ተወጡ። የሱልጣኑን መሸሸጊያ አወደሙ። በዚህ ጦርነትም ኢማሙ 30 ፈረስና ሌሎች ቁሳቁሶችን ማረኩ። ነገር ግን ኢማሙ ሐረር ገብተው ብዙ ሳይቆዩ ሱልጣኑ ለቁጥር የሚያዳግት ሰራዊት እዛው ሶማሌያ ላይ ሰበሰበና ኢማሙን ለማጥቃት ወደ ሐረር ተመመ። የሱልጣኑ ጦር በርካታ ፈረሰኞችን ያካተተ ስለነበር ኢማሙ የሱልጣኑን መቃረብ ሲሰሙ ስልታዊ ማፈግፈግን መረጡ። ከነጦራቸውም ወደ ሁበት ተጉዘው ጋረሙለታ ተራራ ላይ መሸጉ። ሱልጣኑም ሐረር ገባ። ኢማም አሕመድ በጋሪሙለታ ተራራ ላይ መስፈራቸውን የሰማው ሱልጣን ጦሩን ይዞ ሁበት ገባ። ተራራውንም ለቁጥር ባዳገተው ሰራዊት አስከበበው። ከፍተኛ ጥበቃም አደረገ። የኢማሙ ጦር ከተራራው መውረድና ለህይወት መሠረታዊ የሆኑትን ምግብና የመጠጥ ውሀ ማግኘት አልቻሉም። ሱልጣኑ በዚህ ሁኔታ ለሁለት ሳምንታት ያህል ከበባውን አጠናክሮ ቀጠለ። በስተመጨረሻ ግን የኢማሙ ጦር ተዳከመና ተስፋ መቁረጥ ታየ። ስለሆነም በለሊት የኢማሙ ጦር ወርዶ ከሱልጣኑ ጋር ጦርነት ገጠሙ። ዳሩ ግን የኢማሙ ጦር ለ2 ሳምንት ታግቶ የቆየ በመሆኑ ውጊያው ላይ ቀልጣፋ መሆን አልቻለም። በመሆኑም የኢማሙ ጦር በከፍተኛ ሁኔታ ተጠቃ። ከአንጋፋ የኢማሙ የጦር አዝማቾች መካከል አንዱ ዑመረዲንም ተገደለ። ኢማሙና ጥቂት ጓዶቻቸው ግን አመለጡ። የኋላ ኋላ ግን በዘመኑ ዑለማኦች ከፍተኛ ጥረት በሁለቱ አሚሮች መካከል ስምምነት እንዲኖር ተደረገ። ስምምነቱም ሱልጣኑ ሸሪዓን ሊጠብቅና በፍትህ ሊያስተዳድር ኢማሙና ጦራቸው ደግሞ መሸፈቱን አቁሞ ለሱልጣኑ ታዛዥ ሆኖ በሰላም እንዲኖር የሚያግባባ ነበር። ስምምነቱም መተግበር ተጀመረ። ኢማሙም ጥማታቸው የስልጣን ሳይሆን የሸሪዓ መጠበቅ መሆኑን ሰጥ ለጥ ብለው ለሱልጣኑ በመታዘዝ አሳዩ። በኋላ ግን ሱልጣኑ ስምምነቱን አፈረሰ። ቀደምት ዓመታት ኢማም ግራኝ አህመድ የተወለደው ዘይላ ተብላ ትታወቅ በነበረው የባህር በር አካባቢ በሰሜናዊ ምዕራብ አዳል ( በአሁኑ ዘመን ሶማሊያ) ነበር። ይህ ታሪካዊ አዳል (ሶማሊያ) የእስልምና ሃይማኖትን የሚከተል መንግስት ይሁን እንጂ በጊዜ ለነበረ የክርስትና ተከታይ ኢትዮጵያው መካከለኛ መንግስት ግብር ይከፍል ነበር። ግራኝም በጎለመሰ ጊዜ ማህፉዝ የተባለን የዘይላ አስተዳዳሪን ልጅ ባቲ ድል ወምበሬ አገባ።. ነገር ግን ማህፉዝ ከመካከለኛው የኢትዮጵያ መንግስት ተጣልቶ በአጼ ልብነ ድንግል ላይ ጥቃት አድርሶ ሲመለስ በ1517 ተገደለ። በአዳል እርስ በርስ ጦርነት ተነሳ። ግራኝ አህመድም ከተወሰኑ የትግል ዓመታት በኋላ በስልጣን የሚሻኮቱትን በማሸነፍ ሐረርን ተቆጣጠረ። በዚህ ጊዜ የአዳል መሪ ሆነ። በ1527፣ የአዳል መሪ ከሆነ በኋላ፣ ከአዳል ከትሞች የሚጠበቀውን ግብር ለመካከለኛው የኢትዮጵያ መንገስት እንዳይከፈል አገደ። አጼ ልብነ ድንግልም የባሌ ጦር አዛዡን ደግላን ግብሩን እንዲያስከፍል ላከ። ደግላን ግን በአዲር ጦርነት ተሸነፈ። ከዚህ ቀጥሎ ግራኝ ወደ ምስራቅ በመዝመት ሱማሌውችን በጦርነት ግዛቱ አደረገ። ቀስ ብሎም ወደ ምዕራቡ የኢትዮጵያ ክፍል ብዙ ዘመቻወችን በማካሄድ ስፍር ቁጥር የሌላችቸው ባሪያወችን በመፈንገል በደቡብ አረቢያ፣ ለዘቢድ አስተዳዳሪ በስጦታ መልክ በመላክ በተራው የብዙ ጠመንጃወች ባለቤት ሆነ። በ1528 የልብነ ድንግል ሰራዊት በአዳል ላይ ጥቃት ስላደረሰ፣ ይህን ለመበቀል በ1529 በክርስትያኑ ንጉስ ላይ ኢማም አህመድ ዘመቻውን የኢትዮጵያና አዳል ጦርነት ጀመረ። መሰረታዊው የኢማም አህመድ አላማ ግን "ጅሃድ" ወይም "በሃይማኖት መታገል" ነበር ። በዚህ ጊዜ የአጼ ልብነ ድንግልን ሰራዊት መምጣት የሰሙት የግራኝ ወታደሮች በፍርሃት ተውጠው ለመሸሽ ሲሞክሩ፣ ግራኝ ግን በጽናትና ቆራጥነት አብዛኞቹ ባሉበት እንዲቆሙ በማድረግ የልብነ ድንግልን ሰራዊት ከአዲስ አበባ 80 ኪሎ ሜትር ደቡብ ምስራቅ በምትገኘው በሽምብራ ቁሬ ጦርነት መጋቢት 1529 አሸነፈ ። ጦርነቱን ያሸንፍ እንጂ ብዙ ወታደሮች ስላለቁበት ቀሪው ሰራዊቱ ወደሃገሩ ተመልሶ ከንደገና መታገል ሰጋ። በዚህ መሃል ከአረብ አገር 70 ሙሉ ትጥቅ ያላቸው ወታደሮችና ብዙ ጠብመንጃወች እና 7 መድፎች ከኦቶማን ቱርኮች አገኘ። በ1531፣ የግራኝ ጦር የልብነ ድንግልን ሰራዊት አምባሰል አንጾኪያ ላይ ገጥሞ እንደገና ድል አደረገ። ለዚህ ድል መሰረቱ በዕርዳታ ያገኘው መድፍ እንደነበር ሉዶልፍ ሲያትት ከግራኝ ወገን የተተኮሰ መድፍ ጥይት በአጋጣሚ ልብነ ድንግል ሰራዊት መካከል ወደቀ፣ ይህ እንግዳ መሳሪያ የሚያሰክትለውን ቁስል እንኳ እንዴት ማዳን እንደሚቻል የማያውቁጥ ኢትዮጵያውያን በድንጋጤ ተበታተኑ ። ከዚህ በኋላ የኢማሙ ሰራዊት ወደሰሜን በመዝመት በሃይቅ፣ ወሎ ደሴቶች ላይ የነበሩትን አካባቢዎችን ተቆጣጠረ። ቀጥሎም ትግራይ ውስጥ ይጠብቀው የነበረውን ሰራዊት በማሸነፍ አክሱም ከተማ ተቆጣጠረ። ይህ ከመሆኑ በፊት አስቀድማ ንግስት እሌኒ የተባለችው የሃድያ ንግስት ( የዘርዓ ያዕቆብ ሚስት)፣ ለፖርቱጋሎች የወታደር እርዳታ እንዲያረጉ መልዕክት ልካ ኖሮ፣ ታህሳስ 10፣ 1541 400 ጠመንጃ ያነገቱ የፕርቱጋል ሰራዊት ምጽዋ ላይ አረፉ። በዚህ ጊዜ አጼ ልብነ ድንግል በስደት እያለ በ1540 ሲሞት እሱን ተክቶ አጼ ገላውዲወስ ንጉሰ ነገስት ሆኖ ነበር። በ ክሪስታቮ ደጋማ የሚመራው የፖርቹጋሎቹ ሰራዊትና ኢትዮጵያውያን ሚያዚያ 1፣ 1542 በጃርቴ ጦርነት (ጃርቴ በሌላ ስሙ አናሳ ሲባል በአምባላጌ እና በአሻንጌ ሃይቅ መካከል የሚገኝ ቦታ ነው) ከ ግራኝ ሰራዊት ጋር የመጀምሪያ ፍልሚያ አደረገ። በዚህ ጊዜ ፖርቱጋሎቹ ግራኝን ለመጀመሪያ ጊዜ ማየታቸው ሲሆን በጊዜው የነበረው ፖርቹጋላዊው ካስታንሶ ክሩቅ ሆኖ ስላየው ስለግራኝ እንዲህ ይላል፦ በሱ በኩል ያለውን የጦር አውድማ በሚዘጋጅበት ጊዜ፣ የዘይላው ንጉስ ኢማም አህመድ ኮረብታው ላይ ወጣ። በዚህ ጊዜ ብዙ ፈረሰኞች አብረው ተከትለውት ነበር፣ እግረኞችም እንዲሁ። የእኛን የጦር ቀጠና ለመመርመር፣ እኮረብታው ጫፍ ሲደረስ ከ300 ፈረሶች እና ሶስት ግዙፍ ባንዲራወች ጋር ቆመ። አርማዎቹም ሁለቱ ነጭና መካከላቸው ላይ ቀይ ጨረቃ ምልክት ሲኖራቸው አንዱ ደግሞ ቀይና መሃሉ ላይ ነጭ ጨረቃ ያሉባቸው ከንጉሱ ዘንድ ምንጊዜም የማይለዩ ነበሩ ይላል። በዚህ ሁኔታ ለ4 ቀናት በመፋጠጥና መልዕክት በመለዋወጥ እኒህ የማይተዋወቁ ሁለት ሰራዊት ጊዜያቸውን ካሳለፉ በኋላ ክሪስታቮ ደጋማ እግረኛ ወታደሮቹን (ኢትዮጵያኖችንም ይጨምራል) በአራት ማዕዘን ቅርጽ በማደራጀት ወደ ኢማሙ ሰራዊት ዘመተ። የእስላሙ ሰራዊት፣ ብዙ ጊዜ እየደጋገመ ጥቃት ቢያደረስም በመድፍና በጠመንጃ የታጠረ አራት ማዕዘኑ ሊሸነፍ አልቻለም። በዚህ ጦርነት መካከል በድንገት በተተኮሰ ጥይት ግራኝ አህመድ እግሩ ላይ ቆሰለ። ስለሆነም የኢማሙ ሰራዊት መሸሽ መጀመሩን ያዩት የኢትዮጵያና የፖርቹጋል ሰራዊት ተበታትኖ የሚሮጠውን ሰራዊት በማጥቃት ከፍተኛ ጉዳት አደረሱ። ይሁንና የቀሩት ወታደሮች ከእንደገና በማደራጀት ኢማሙ ጦርነት ከተካሄደብት ወንዝ ራቅ ብሎ ሰፈረ። በሚቀጥሉት ጥቂት የግራኙ ጎራ አዳዲስ ወታደሮች በማስመጣት በከፍተኛ ሁኔታ መጠናከር ጀመረ። ይህ ነገር ያላማረው ደጋማ ቶሎ ብሎ ጦርነት መግጠም አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ መጋቢት 16 ላይ አሁንም አራት ማዕዘን በመስራት ዘመተ። ምንም እንኳ የኢማሙ ጦር ከበፊቱ በበለጠ ቁርጠኝነት ቢዋጉም፣ በድንገት በፈነዳ የጥይት ቀልህ ምክንያት ፈረሶቹ በመደናገጣቸው አራቱ ማዕዘን አሁንም አሸነፈ። በዚህ ጊዜ የኢማሙ ሰራዊት በዕውር ደንብስ እያመለጠ ሸሸ። ክሳታንሶ የተባለው ፖርቱጋላዊም በጸጸት እንዲህ ብሎ መዘገበ፡ መቶ የሚሆኑ ፈረሶች ቢኖሩን ኑሮ የዛሬው ቀን ድል የተሟላ ይሆን ነበረ ምክንያቱም ንጉሱ እራሱ በቃሬዛ አራት ሰወች ተሸክመውት ነው ያመለጠው። ቀሪው ሰራዊትም የሸሸው በተረጋጋ ሁኔታ ሳይሆን በእውር ድንብስ ነበር። የመረብ ምላሽ (አሁኑ ኤርትራ) አስተዳዳሪ ባህር ንጉስ ይስሃቅ ከተደባለቀ በኋላ፣ አጠቃላዩ ሰራዊ ወደ ደቡብ በመነቀሳቀስ በ10ኛው ቀን ከግራኙ ጦር ፊት ለፊት አረፈ። በዚህ መሃል ክረምት ስለገባ በዝናቡ ምክንያት ደጋማ ለሶስተኛ ጊዜ ግራኝን ሊገጥመው ፈልጎ ግን ሳይችል ቀረ። በንግስት ሰብለ ወንጌል ጎትጓችነት ደጋማ በወፍላ፣ ከአሻንጌ ሃይቅ ፊት ለፊት፣ ከግራኝ ጦር ብዙም ሳይርቅ ክረምቱን አሳለፈ። በዚህ ትይዩ ኢማሙ ደግሞ በ ዞብል ተራራወች ላይ ሰራዊቱን አስፈረ። ድል በጦር መሳሪያ ብዛት እንደሚወሰን የተገነዘበው ግራኝ ለእስላሙ አለም የድረሱልኝ ጥሪ አቀረበ። አረቦችም 2000 ጠመንጃወችና መድፎች እንዲሁም ከቱርክ 900 የተመረጡ ወታደሮች ተላኩለት። ባንጻሩ የፖርቹጋሎቹ ወታደሮች ብዛት በተለያዩ ግዴታወችና በጦርነት ላይ በደረሰው ሞት ምክንያት ከ400 ወደ 300 ዝቅ ብሎ ነበር። ይህ በዚህ እንዳለ ክረምት አልፎ በጋ ሲሆን በሃይል የተጠናከረው ግራኝ አህመድ በፖርቹጋሎቹ የጦር ቀጠና ላይ ጥቃት በማድረስ ቁጥራቸውን ወደ 140 አመናመነው። ክርስታቮ ደጋማም ቆስሎ 10 ከሚሆኑ ወታደሮቹ ጋር ተማረከ። በዚህ ጊዜ በሃይማኖቱ ከጸና እንደሚገደል ከሰለመ ግን እንደማይገደል ተነግሮት ሃይማኖቴን አልቀይርም በማለቱ በተማረክበት ተገደለ። ከዚህ ጥቃት የተረፉትና የአጼ ገላውዲወስ ሰራዊት በመጨረሻ ተገናኝተው ሃይላቸውን በማጠናከር የካቲት 21፣ 1543 የወይና ደጋ ጦርነት ተብሎ በሚታወቀው ጥቃት አደረሱ። በዚህ ጦርነት 8560 የሚሆኑት የኢትዮጵያና ፖርቱጋል ሰራዊት 15,200 የሚሆነውን የኢማሙን ሰራዊት አሸነፈ። ኢማሙ በጥይት ተመትቶ ለማምለጥ ሲሞክር ካልአይ የተባለ ወጣት የፈረሰኛው ጦር መሪ ተከታትሎ ሄዶ አንገቱን ቀልቶ ገደለው። የግራኝ ሚስት፣ ባቲ ድል ወምበሬም ከተራረፉ የቱርክ ወታደሮች ጋር አምልጣ ሐረር ገባች። ተከታዮቿንም በማስተባበር የባሏን ሞት ለመበቀል የባሏን እህት ልጅ ኑር ኢብን ሙጃሂድን በማግባት ተነሳች። ፈጠገር ውስጥ የኑር ኢብን ሙጃሂድወታደሮች ጋር ሲዋጋ አጼ ገላውዲወስ እንደተገደለ እና አስከሬኑ ተፈልጎ አንገቱ ተቆርጦ ወደ ሐረር እንደተላከ አንዳንድ የታሪክ ጸሓፊያን ይዘግባሉ:: አቤቶ ሀመልማል የተባለው የአፄ ገላውዴዎስ አጎት ልጅ ሰራዊቱን እየመራ ሀረር ከተማ ገብቶ ከተማይቱን ከዘረፈ እና ካወደመ በኋላ ሱልጣን በረከትን ማርኮ አንገቱን ቀልቶ እደገደለውም ተፅፏል። የኢትዮጵያ ታሪክ ግራኝ አህመድ ፉቱሑል ሐበሻ ሺሃቡዲን ኣረብ ፈቂህ ሷሊሕ አስታጥቄ የፌስ ቡክ ገፅ
22875
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%A5%E1%88%AD%E1%8A%9D
ጥርኝ
ጥርኝ (ሮማይስጥ፦ ) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ አጥቢ እንስሳ ነው። ጥርኞች ከአፍሪቃ የሸለምጥማጥና ጥርኝ አስተኔ ዘመድ ውስጥ በመጠን ትልቆቹ ናቸው። የእንስሳው የተፈጥሮ ሁኔታና ባሕርይ ክብደታቸው ከ፯ እስከ ፳ ኪሎግራም፣ ከፍታቸው ከ፴፭ እስከ ፵ ሴንቲሜትር፣ ከጅራታቸው በስተቀር ርዝመታቸው ከ፷፰ እስከ ፹፱ ሴንቲሜትር የሆነ ሥጋ በሎች ናቸው። ጅራታቸው የጠቅላላ አካላቸውን ርዝመት ሢሦ ይሆናል። በመጠን ወንዶቹ ጥርኞች ከሴቶቹ ይበልጣሉ። ፈርጠም ያሉ ቅልጠሞቻቸው ከሌሎቹ የዘመዱ አባሎች ይልቅ ረዘም ያሉ፣ ታፋቸው ከፍ ብሎ የኋላ እግሮቻቸው ከፊተኞቹ የበለጠ ጠንካራ የሆኑ፣ በያንዳንዱ እግር አምስት ጣቶች ያሏቸው፣ እያንዳንዱ ጣት ዱልዱም ኮኮኔ ያለው እንስሳ ነው። ጥርኞች ጥርሶቻቸው ትላልቅ ሆነው እንደ ውሻ ሁሉ ሰፋፊ የመንጋጋ ጥርሶች አሏቸው። ጆሮዎቻቸው ሰፋፊ ናቸው።የቆዳቸው ፀጉር ግራጫ ሆኖ ጥቋቁር መስመሮችና ረጃጅም ነጠብጣቦች አሉት። አንገታቸው ላይ ሁለት ጥቋቁር መስመሮች አሏቸው። ልጆቻቸው ጥቁር ቡናማ ቀለም ሲኖሯቸው ምልክቶቹ ግን አይለዩም። ትልቅ የእዥ ዕጢና የቂጥ ከረጢት ዕጢ አላቸው። ጥርኞች ለስሪያ ከአካባቢያቸው ርቀው ሊሄዱ ይችላሉ። ከወትሮው በተለየ ይንቀዠቀዣሉ። ወንዱ የሴቷን ዝባድና ሽንት እያሸተተና ሽቅብ እያነፈነፈ የመቀበል ጊዜዋ መድረሱን ያረጋግጣል። በመጀመሪያ ሴቷ በቁጣ ስታባርረው ወንዱ በተሸናፊነት ይመለሳል። ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ የሆነችው ሴት በወንዱ አጠገብ በመሮጥ እንዲከተላት ትቆሰቁሰዋለች። በስሪያ ጊዜ ከታፋዋ ከፍ አድርጋ በፊት እግሮቿ ላይ ትተኛለች። ሴቱቱ ጮሃ ወደፊት ለመንቀሳቀስ ከፈለገች ወንድየው የአንገቷን ጸጉር በጥርሱ ጨምድዶ ይገታታል። አንድ ደቂቃ ያህል ከሚፈጀው ስሪያ በኋላ ሁለቱም ብልቶቻቸውን ይልሳሉ። ጥርኞች ከአንድ እስከ አራት ቡችሎችን በጉድጓድ ውስጥ ይወልዳሉ። የቡችሎቹ ዓይኖች ሲወለዱ ወይም በጥቂት ቀኖች ውስጥ ይከፈታሉ። በአምሥት ቀኖች ውስጥ መራመድ ይችላሉ። ሆኖም ከጉድጓዳቸው የሚወጡት በሥስተኛው ሳምንት ነው። በሁለት ሳምንት ውስጥ እርስ በርስ መጫወት ይጀምራሉ። እያንዳንዱ ቡችላ አንድ ጡት ይጠባል። እናቶች ከአንድ ወር ጀምረው ጡት ማስጣል ይጀምሯቸዋል። ሆኖም ጨርሰው መጥባት የሚተዉት ከ፲፬ እስከ ፳ ሳምንት ሲሞላቸው ነው። በአምስተኛው ወር ዝባድ ማውጣት ይጀምራሉ። በዚህ ወቅት ወንዶቹ ቡችላዎች ምልክት ማድረግና ሽንት ማሽተት ይጀምራሉ። የቆለጣቸውም መጠን ትልቅ እየሆነ ይሄዳል። በሰው ቁጥጥር ስር ሆነው በዓመት ሦስት ጊዜ የሚወልዱ መሆናቸው ቢታወቅም በተፈጥሮ ሁኔታ የሚወልዱት ክረምት ሲጀምር ነው። አንድ ዓመት የሞላት ጥርኝ ማርገዝ ትችላለች። ከወለደች ከሦስት ወር ተኩል በኋላም እንደገና ማርገዝ ትችላለች። የእርግዝናቸው ጊዜ ወደ ፹ ቀኖች ግድም ነው። ማኅበራዊ አደረጃጀታቸው ብቸኛ፣ ሌቴ፣ እና ምናልባትም ክልልተኛ ነው። ቀን ቀን በጉድጓዶችና ጥቅጥቅ ባለ ጥሻ ይጠለላሉ። ቀን በግልፅ የሚታዩት አልፎ አልፎ ብቻ ነው። ጥርኞች በአንድ ሥፍራ ተወስነው የሚኖሩ፤ ምግባራቸው የማይለዋወጥ አልፎ አልፎ ምልክት ባደረጉበት መንገድ የሚጓዙ እንስሶች ናቸው። ምንም እንኳ የሽታ ምልክት ማድረጋቸውና ዓይነ ምድራቸውን በተወሰኑ የድንበር ሥፍራዎች መጣላቸው የታወቀ ቢሆንም ክልልተኛው ወንዱ ብቻ ይሁን ወይስ ሴቷም ጭምር የታወቀ ነገር የለም። የተያዙ ጥርኞች በስሪያ ጊዜ መጣላታቸው እንዲሁም የቡችሎቻቸው የጨዋታ ትግል ወደ ምር ፀብ መለወጡ ማኅበራዊ አለመሆናቸውን ያመለክታሉ። ወንድና ሴት አብረው የሚገኙት ለስሪያ ብቻ ነው። ጥርኞች ማታ ለአደን ሲወጡ ጸጥ ብለው ራሳቸውን ወደ መሬት ደፍተው እጅግ ጥሩ የሆነውን የማሽተትና የመስማት ኃይላቸውን በመጠቀም ጥሻ ውስጥ ያሉትን ታዳኞች ለማግኘት ይጥራሉ። ጥርኞች የሚያድኑት እንደ ሸለምጥማጥ አድፍጠውና አሳደው ሳይሆን በያሉበት ቀጨም እያደረጉ ነው። ጥርኞች የሚያድኑትን ሁሉ የሚይዙት አገጫቸውን ተጠቅመው ቢሆንም የአጠቃቅ ዘዴያቸው እንደታዳኙ መጠንና የመከላከል ችሎታ ይለያያል። አይጥና እባብን የመሰሉት ሲገድሉ፣ ነክሰው በኃይል በመነቅነቅ የጀርባ አጥንቶቻቸውን በመሰባበር ነው። ተለቅ ያለ እንስሳ ሲሆን የራስ ቅሉን በጽኑ በመንከስ ነው። ጥርኞች ሲበሉ እየተጣደፉ ነው፤ ሲውጡም በደንብ ሳያኝኩ ነው። ጥርኞች ለምግብ ፍለጋ ቀስ ብለው ቢራመዱም ሲያስፈልግ በፍጥነት መሮጥ ይችላሉ። እስከ ግማሽ ሜትር ያህል ከፍታ እየሮጡ መዝዘል ይችላሉ። ብዙ ጊዜ ግን ከመሮጥ ይልቅ ወደሚሸሸጉበት ጥሻ እጥፍ ማለትን ያዘወትራሉ። የመኖሪያው መልክዓ ምድር እጅግ በረሃማ ከሆኑ ሥፍራዎች በስተቀር በቂ ሽፋን ባለበት ቦታ በመላው አፍሪቃ ይገኛሉ። ብዙ ጊዜ ውኃ ካለበት ሥፍራ አይርቁም። በአካሉ መዋቅር የተነሳ ምድቡ ከሥጋ በሎች ቢሆንም ጥርኝ ሥጋም ሆነ ዕፅ ያገኘውን የሚበላ እንስሳ ነው። የተለያዩ ዕፅዋትን፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ሦስት አፅቄዎችና ሌሎች የጀርባ አጥንት የሌላቸው እንስሳትን ይበላሉ። የጀርባ አጥንት ካላቸውም ውስጥ አዲስ የተወለዱ አነስተኛ የቀንድ እንስሳት ጭምር አድነው ይበላሉ። ጥንብም ይበላሉ። የእንስሳው ጥቅም በቂጥ ከረጢት እዣቸው ምልክት የሚያደርጉት በመንገዳቸው ዳር ያሉ ዛፎች ግንዶች ላይ ነው። በተለይም ፍሬውን የሚበሉት ዛፍ ላይ በየ ፹፭ ሜትሩ ገደማ በዚህ እዥ ምልክት ያደርጋሉ። ይህ እዥ ዝባድ ይባላል። ወፈር ያለ፣ ቢጫ ቅባት ዓይነት ነው። እየቆየ ሲሄድ ግን ይጠጥርና ጥቁር ቡኔ ይሆናል። ሽታው ደግሞ እስከ አራት ወር ይቆያል። ተይዘው የሚገኙ ጥርኞች አልፎ አልፎ በየጊዜው ዝባድ ይጨለፍባቸዋል። ዝባድ ሴቬቶን ወደሚባል ውሕድ ይጣራና ውድ የሆኑ ሽቶዎች የሚሠሩ ፋብሪካዎች ይጠቀሙበታል። ወንዶቹም ሴቶቹም በጣም የሚሸተውን ዓይነ ምድራቸውን በአንድ ሥፍራ ይጥላሉ። በሽንታቸው ምልክት የሚያደርጉት ግን ወንዶቹ ብቻ ናቸው። ዋቢ ምንጭ- ሪፖርተር ፤«ጥርኝ (»፤ ሰሎሞን ይርጋ (ዶር.) ‹‹አጥቢዎች›› የኢትዮጵያ አጥቢ እንስሳት የዱር አራዊት
52425
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8C%8A%E1%8B%9B%20%E1%89%B3%E1%88%8B%E1%89%85%20%E1%8D%92%E1%88%AB%E1%88%9A%E1%8B%B5
የጊዛ ታላቅ ፒራሚድ
ታላቁ የጊዛ ፒራሚድ (የኩፉ ፒራሚድ ወይም የቼፕስ ፒራሚድ በመባልም ይታወቃል) በጊዛ ፒራሚድ ኮምፕሌክስ የዛሬ ጊዛን በታላቁ ካይሮ፣ ግብፅ ውስጥ ከሚገኙት ፒራሚዶች ሁሉ ጥንታዊ እና ትልቁ ነው። ከጥንታዊው ዓለም ሰባቱ አስደናቂ ነገሮች ውስጥ እጅግ ጥንታዊው ነው፣ እና በብዛት ሳይበላሽ የቀረው ብቸኛው። የግብፅ ተመራማሪዎች ፒራሚዱ ለአራተኛው ሥርወ መንግሥት የግብፅ ፈርዖን ኩፉ መቃብር ሆኖ እንደተሠራ እና በ26ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. በ27 ዓመታት አካባቢ እንደተገነባ ይገምታሉ። መጀመሪያ ላይ 146.5 ሜትር (481 ጫማ) ላይ የቆመው ታላቁ ፒራሚድ በአለም ላይ ከ3,800 ዓመታት በላይ ረጅሙ ሰው ሰራሽ መዋቅር ነበር። በጊዜ ሂደት፣ አብዛኛው ለስላሳ ነጭ የኖራ ድንጋይ መከለያ ተወግዷል፣ ይህም የፒራሚዱን ቁመት አሁን ወዳለው 138.5 ሜትር (454.4 ጫማ) ዝቅ አድርጎታል። ዛሬ የሚታየው ከስር ያለው ዋና መዋቅር ነው. መሰረቱ የተለካው ወደ 230.3 ሜትር (755.6 ጫማ) ካሬ ሲሆን ይህም መጠን በግምት 2.6 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር (92 ሚሊዮን ኪዩቢክ ጫማ) ሲሆን ይህም ውስጣዊ ሂሎክን ያካትታል። የፒራሚዱ ስፋት 280 ንጉሣዊ ክንድ (146.7 ሜትር፣ 481.4 ጫማ) ቁመት፣ የመሠረቱ ርዝመት 440 ክንድ (230.6 ሜትር፣ 756.4 ጫማ)፣ 5+ ሰከንድ መዳፎች (የ 51°50'40 ቁልቁል)። ታላቁ ፒራሚድ በድምሩ 6 ሚሊዮን ቶን የሚመዝኑ 2.3 ሚሊዮን የሚገመቱ ትላልቅ ብሎኮችን በመቆፈር የተገነባ ነው። አብዛኛዎቹ ድንጋዮች በመጠን እና በቅርጽ አንድ ወጥ አይደሉም እና በጣም የለበሱ ብቻ ናቸው። የውጪው ንብርብሮች በሙቀጫ አንድ ላይ ተጣብቀዋል. በዋነኛነት ከጊዛ ፕላቱ የተገኘ የኖራ ድንጋይ ጥቅም ላይ ውሏል። ሌሎች ብሎኮች በአባይ ወንዝ ላይ በጀልባ ይገቡ ነበር፡ ነጭ የኖራ ድንጋይ ከቱራ ለመያዣ፣ እና ከአስዋን እስከ 80 ቶን የሚመዝኑ ግራናይት ብሎኮች ለንጉሱ ቻምበር መዋቅር። በታላቁ ፒራሚድ ውስጥ ሶስት የታወቁ ክፍሎች አሉ። ዝቅተኛው ፒራሚዱ የተገነባበት አልጋ ላይ ተቆርጧል, ነገር ግን ሳይጠናቀቅ ቀረ. የንግስት ቻምበር እና የንጉስ ክፍል እየተባለ የሚጠራው፣ ግራናይት ሳርኮፋጉስ ያለው፣ በፒራሚድ መዋቅር ውስጥ ከፍ ያለ ነው። የኩፉ ቪዚየር ሄሚዩን (ሄሞን ተብሎም ይጠራል) በአንዳንዶች የታላቁ ፒራሚድ መሐንዲስ እንደሆነ ይታመናል። ብዙ የተለያዩ ሳይንሳዊ እና አማራጭ መላምቶች ትክክለኛውን የግንባታ ቴክኒኮችን ለማብራራት ይሞክራሉ። በፒራሚዱ ዙሪያ ያለው የቀብር ሥነ ሥርዓት በአንድ መንገድ (ከፒራሚድ አቅራቢያ አንዱ እና በናይል ወንዝ አቅራቢያ) የተገናኙ ሁለት የሬሳ ቤተመቅደሶችን ያቀፈ ነው ፣ የቅርብ ቤተሰብ እና የኩፉ ፍርድ ቤት መቃብሮች ፣ ለኩፉ ሚስቶች ሦስት ትናንሽ ፒራሚዶችን ጨምሮ ፣ የበለጠ ትንሽ " የሳተላይት ፒራሚድ" እና አምስት የተቀበሩ የፀሐይ ጀልባዎች. የኩፉ መለያ በታሪክ ታላቁ ፒራሚድ ለኩፉ የተነገረው በጥንታዊ ጥንታዊነት ደራሲዎች ቃል ላይ በመመስረት ነው፣ በመጀመሪያ ደረጃ ሄሮዶተስ እና ዲዮዶረስ ሲኩለስ። ነገር ግን፣ በመካከለኛው ዘመን ሌሎች በርካታ ሰዎች ለፒራሚዱ ግንባታ እውቅና ተሰጥቷቸው ነበር፣ ለምሳሌ ዮሴፍ፣ ናምሩድ ወይም ንጉስ ሳሪድ። እ.ኤ.አ. በ 1837 ከንጉሱ ቻምበር በላይ አራት ተጨማሪ የእርዳታ ክፍሎች ከነሱ ጋር ከተገናኙ በኋላ ተገኝተዋል ። ክፍሎቹ, ቀደም ሲል ሊደረስባቸው የማይችሉት, በቀይ ቀለም በሂሮግሊፍስ ተሸፍነዋል. ፒራሚዱን የሚገነቡት ሠራተኞች የፈርዖንን ስም የሚያጠቃልል የቡድናቸው ስም (ለምሳሌ፡ “ወንበዴው፣ የክኑም-ኩፉ ነጭ ዘውድ ኃይለኛ ነው”) ብሎኮችን በቡድናቸው ስም አስፍረዋል። የኩፉ ስሞች ከደርዘን በላይ ጊዜ በግድግዳዎች ላይ ተጽፈዋል። ከእነዚህ የግራፊቲ ጽሑፎች ውስጥ ሌላው በፒራሚዱ 4ኛ ንብርብር ውጫዊ ክፍል ላይ በጎዮን ተገኝቷል። ፅሁፎቹ በሌሎች የኩፉ ቦታዎች ላይ ከሚገኙት ጋር የሚነፃፀሩ ናቸው ለምሳሌ በ ላይ ያለው አልባስተር ቋሪ ወይም በዋዲ አል-ጃርፍ ወደብ እና በሌሎች ፈርዖኖች ፒራሚዶች ውስጥም ይገኛሉ። በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን ከፒራሚዱ አጠገብ ያሉት የመቃብር ቦታዎች ተቆፍረዋል. የኩፉ ቤተሰብ አባላት እና ከፍተኛ ባለስልጣናት የተቀበሩት በምስራቅ ፊልድ ከመንገድ በስተደቡብ እና በምእራብ ሜዳ ነው። በተለይም የኩፉ ሚስቶች ፣ልጆች እና የልጅ ልጆች ፣ሄሚኑ ፣አንካፍ እና (የቀብር መሸጎጫ) ሄቴፌሬስ 1 ፣ የኩፉ እናት። ሀሰን እንደተናገረው፡- “ከመጀመሪያዎቹ የስርወ መንግስት ዘመናት ጀምሮ ዘመዶቻቸው፣ ጓደኞቻቸው እና የቤተ መንግስት አስተዳዳሪዎች በህይወት እያሉ ሲያገለግሉት በነበሩት ንጉስ አካባቢ መቀበር የተለመደ ነበር። ከዚህ በኋላ." የመቃብር ስፍራዎቹ እስከ 6ኛው ሥርወ መንግሥት ድረስ በንቃት ተዘርግተው ከዚያ በኋላ ብዙም ጥቅም ላይ አልዋሉም። የመጀመርያው የፈርዖን ስም የማኅተም ግንዛቤዎች የኩፉ፣ የፔፒ የቅርብ ጊዜ ነው። የሠራተኛ ግራፊቲ በአንዳንድ የመቃብር ድንጋዮች ላይም ተጽፎ ነበር; ለምሳሌ፣ "" (የኩፉ ሆረስ ስም) በቹፉናክት ማስታባ ላይ፣ ምናልባትም የኩፉ የልጅ ልጅ። በማስታባስ የጸሎት ቤቶች ውስጥ ያሉ አንዳንድ ጽሑፎች (እንደ ፒራሚዱ፣ የመቃብሪያ ክፍሎቻቸውም አብዛኛውን ጊዜ የተቀረጹ ጽሑፎች የሌላቸው ነበሩ) ኩፉ ወይም ፒራሚዱን ይጠቅሳሉ። ለምሳሌ፣ የመርስያንክ ሳልሳዊ ጽሑፍ “እናቷ [የላይኛው እና የታችኛው ግብፅ የኩፉ ንጉስ ልጅ ነች” ይላል። ብዙ ጊዜ እነዚህ ማጣቀሻዎች የማዕረግ አካል ናቸው፣ ለምሳሌ፣ ፣ “የመቋቋሚያ ዋና አስተዳዳሪ እና የአክሄት-ኩፉ ፒራሚድ ከተማ የበላይ ተመልካች” ወይም መሪብ “የኩፉ ካህን”። በርካታ የመቃብር ባለቤቶች የንጉሥ ስም እንደየራሳቸው ስም አካል አላቸው (ለምሳሌ ቹፉድጀዴፍ፣ ቹፉሴንብ፣ መሪቹፉ)። በጊዛ የተጠቀሰው የመጀመሪያው ፈርዖን ሰኔፍሩ (የኩፉ አባት) ነው። እ.ኤ.አ. በ 1936 ሀሰን በጊዛ ታላቁ ሰፊኒክስ አቅራቢያ የአሜንሆቴፕ ን ምስል ገለጠ ይህም ሁለቱ ትላልቅ ፒራሚዶች አሁንም በአዲሱ መንግሥት ለክሁፉ እና ከፋሬ የተሰጡ ናቸው ። እንዲህ ይነበባል፡- “በሜምፊስ ፈረሶችን በማገናኘት ገና በወጣትነቱ፣ እና በሆር-ኤም-አኸት (ስፊንክስ) መቅደስ ላይ ቆመ። የመቅደሱን ውበት በመመልከት በዙሪያው በመዞር ጊዜ አሳለፈ። የኩፉ እና ካፍራ የተከበረው. እ.ኤ.አ. በ 1954 ከፒራሚዱ ደቡባዊ ግርጌ የተቀበሩ ሁለት የጀልባ ጉድጓዶች ፣ አንደኛው ኩፉ መርከብ ተገኘ። የጄደፍሬ ካርቱች የጀልባውን ጉድጓዶች በሚሸፍኑት ብዙ ብሎኮች ላይ ተገኝቷል። እንደ ተተኪ እና የበኩር ልጅ ለኩፉ ቀብር ተጠያቂ ሊሆን ይችላል። ሁለተኛው የጀልባ ጉድጓድ በ 1987 ተመርምሯል. ቁፋሮ ሥራ በ 2010 ተጀምሯል በድንጋዮቹ ላይ ግራፊቲ በ 4 "ኩፉ" ስም, 11 "ድጄደፍሬ", አንድ አመት (በንግሥና, ወቅት, ወር እና ቀን), የድንጋይ መለኪያዎች, የተለያዩ ምልክቶች እና ምልክቶች, እና በግንባታ ላይ ጥቅም ላይ የሚውል የማጣቀሻ መስመር, ሁሉም በቀይ ወይም በጥቁር ቀለም የተሠሩ ናቸው. በ2013 በቁፋሮ ወቅት የሜረር ማስታወሻ ደብተር በዋዲ አል-ጃርፍ ተገኝቷል። ከቱራ ወደ ታላቁ ፒራሚድ የነጭ የኖራ ድንጋይ ብሎኮችን ማጓጓዝን ይመዘግባል። ድንጋዮቹ በሼ አኸት-ኩፉ ("የኩፉ የፒራሚድ አድማስ ገንዳ") እና በሮ-ሼ ኩፉ ("የኩፉ ገንዳ መግቢያ") በአንክሃፍ፣ የግማሽ ወንድም እና ክትትል ስር እንደነበሩ በዝርዝር ይገልጻል። የኩፉ ፣ እንዲሁም የጊዛ ምስራቃዊ መስክ ትልቁ ማስታባ ባለቤት ታላቁ ፒራሚድ ወደ 4600 ዓመታት ያህል ዕድሜ እንዳለው በሁለት ዋና ዋና አቀራረቦች ተወስኗል፡ በተዘዋዋሪም ከኩፉ እና በጊዜ ቅደም ተከተል ዘመኑ በአርኪኦሎጂያዊ እና ጽሑፋዊ መረጃዎች ላይ በመመስረት; እና በቀጥታ፣ በፒራሚዱ ውስጥ በተገኙ እና በሙቀጫ ውስጥ የተካተተው ኦርጋኒክ ቁሳቁስ በሬዲዮካርቦን የፍቅር ግንኙነት። ታሪካዊ ቅደም ተከተል በቀደሙት ዘመናት ታላቁ ፒራሚድ ቀኑ የተነገረው ለክፉ ብቻ በመሆኑ የታላቁን ፒራሚድ ግንባታ በግዛቱ ውስጥ አስቀምጦ ነበር። ስለዚህ ከፒራሚድ ጋር መተዋወቅ ከኩፉ እና ከ 4 ኛው ስርወ መንግስት ጋር የመገናኘት ጉዳይ ነበር። የክስተቶች አንጻራዊ ቅደም ተከተል እና ተመሳሳይነት በዚህ ዘዴ የትኩረት ነጥብ ላይ ይቆማል. ፍፁም የቀን መቁጠሪያ ቀናቶች ከተጠላለፉ የመረጃ መረብ የተገኙ ናቸው፣ የጀርባ አጥንታቸውም ከጥንታዊ የንጉሥ ዝርዝሮች እና ሌሎች ጽሑፎች የታወቁት የተከታታይ መስመሮች ናቸው። የግዛቱ ርዝማኔ ከኩፉ እስከ ቀደም ባሉት ጊዜያት ወደታወቁት ነጥቦች የተጠቃለለ፣ በዘር ሐረግ መረጃ፣ በሥነ ፈለክ ምልከታ እና በሌሎች ምንጮች የተጠናከረ ነው። እንደዚያው፣ የግብፅ ታሪካዊ የዘመን አቆጣጠር በዋነኛነት ፖለቲካዊ የዘመን አቆጣጠር ነው፣ ስለዚህም ከሌሎች የአርኪኦሎጂ ማስረጃዎች እንደ ስትራቲግራፊ፣ ቁሳዊ ባህል ወይም ራዲዮካርበን መጠናናት። አብዛኛው የቅርብ ጊዜ የዘመን አቆጣጠር ግምቶች ኩፉ እና ፒራሚዱ በ2700 እና 2500 ዓክልበ. ራዲዮካርበን የፍቅር ጓደኝነት ሞርታር በታላቁ ፒራሚድ ግንባታ ላይ በብዛት ጥቅም ላይ ውሏል። በማደባለቅ ሂደት ውስጥ ከእሳት የሚወጣው አመድ በሙቀጫ ውስጥ ተጨምሯል ፣ ሊወጣ የሚችል ኦርጋኒክ እና ራዲዮካርቦን ቀንሷል። በ 1984 እና 1995 በአጠቃላይ 46 የሞርታር ናሙናዎች ተወስደዋል, ይህም ከዋናው መዋቅር ጋር በግልጽ የተገጣጠሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ እና በኋላ ላይ ሊካተቱ አይችሉም. ውጤቶቹ በ2871-2604 ዓክልበ. የኦርጋኒክ ቁሳቁሱ ዕድሜ የሚወሰነው ለመጨረሻ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለበት ጊዜ ስላልነበረ የድሮው የእንጨት ችግር ለ 100-300 ዓመታት ማካካሻ በዋናነት ተጠያቂ እንደሆነ ይታሰባል. መረጃው እንደገና ሲተነተን በ2620 እና 2484 ዓክልበ. መካከል ፒራሚዱ የተጠናቀቀበትን ቀን በትናንሾቹ ናሙናዎች ላይ በመመስረት አሳይቷል። እ.ኤ.አ. በ 1872 ዌይንማን ዲክሰን የታችኛውን ጥንድ "አየር-ዘንግ" ተከፈተ ፣ ቀደም ሲል በሁለቱም ጫፎች ተዘግቷል ፣ ቀዳዳዎችን ወደ ንግስት ቻምበር ግድግዳዎች በመቁረጥ ። በውስጡ ከተገኙት ነገሮች አንዱ የዲክሰን ጓደኛ የሆነውን ጄምስ ግራንት የያዘው የዝግባ እንጨት ነው። ከውርስ በኋላ እ.ኤ.አ. በ1946 ለአበርዲን ሙዚየም ተሰጥቷል ፣ነገር ግን ተከፋፍሎ ነበር እና በስህተት ተይዟል። በሰፊው የሙዚየም ስብስብ ውስጥ የጠፋው በ2020 ብቻ ራዲዮካርበን ሲሆን በ3341–3094 ዓክልበ. ከኩፉ የዘመን አቆጣጠር ከ500 አመት በላይ የሚበልጠው አቤር ኢላዳንይ እንጨቱ ከረጅም እድሜ ዛፍ መሃል እንደመጣ ወይም ፒራሚዱ ውስጥ ከመቀመጡ በፊት ለብዙ አመታት እንደገና ጥቅም ላይ ውሎ እንደነበረ ይጠቁማል። የኩፉ እና የታላቁ ፒራሚድ የፍቅር ጓደኝነት ታሪክ በ450 ዓክልበ. ሄሮዶተስ ታላቁን ፒራሚድ ቼፕስ (ሄለናይዜሽን ኦፍ ኩፉ) እንደሆነ ተናግሮ ነበር፣ ሆኖም ግን በራምሳይድ ዘመን በኋላ በስህተት ንግሥናውን አኖረ። ማኔቶ፣ ከ200 ዓመታት በኋላ፣ የግብፅን ነገሥታት ዝርዝር በማዘጋጀት፣ በሥርወ መንግሥት ከፋፍሎ፣ ኩፉን ለ 4ኛ መድቧል። ነገር ግን፣ በግብፅ ቋንቋ ፎነቲክ ከተቀየረ በኋላ እና በግሪክ ትርጉም፣ "" ወደ "ሶፊስ" (እና ተመሳሳይ ስሪቶች) ተቀይሯል። ግሬቭስ፣ በ1646፣ የፒራሚዱ ግንባታ የሚካሄድበትን ቀን የማጣራት ከፍተኛ ችግር መሆኑን ዘግቧል፣ በጎደሉት እና እርስ በርሱ የሚጋጩ ታሪካዊ ምንጮች። ከላይ በተገለጹት የፊደል አጻጻፍ ልዩነቶች ምክንያት፣ በማኔቶ የንጉሥ ዝርዝር ውስጥ ኩፉን አላወቀውም (በአፍሪካነስ እና በዩሴቢየስ እንደተፃፈው)፣ ስለዚህም በሄሮዶተስ የተሳሳተ መለያ ላይ ተመርኩዞ ነበር። የተከታታይ መስመሮችን ቆይታ በማጠቃለል፣ ግሬቭስ 1266 ዓክልበ. የኩፉ የግዛት ዘመን መጀመሪያ እንዲሆን ተጠናቀቀ። ከሁለት መቶ ዓመታት በኋላ፣ በማኔቶ የዘመን አቆጣጠር ውስጥ አንዳንድ ክፍተቶች እና እርግጠኛ ያልሆኑ ነገሮች እንደ ቱሪን፣ አቢዶስ እና ካርናክ በመሳሰሉት የንጉስ ሊስት ግኝቶች ተጠርገዋል። በ1837 በታላቁ ፒራሚድ እፎይታ ክፍል ውስጥ የተገኘው የኩፉ ስም ቼፕስ እና ሶፊስ አንድ እና አንድ መሆናቸውን ግልጽ ለማድረግ ረድተዋል። ስለዚህ ታላቁ ፒራሚድ በ 4 ኛው ሥርወ መንግሥት ውስጥ እንደተገነባ ታወቀ። በግብፅ ተመራማሪዎች መካከል ያለው የፍቅር ግንኙነት አሁንም በበርካታ ክፍለ ዘመናት (ከ4000-2000 ዓክልበ. ግድም) ይለያያል፣ እንደ ዘዴው፣ አስቀድሞ የታሰቡ ሃይማኖታዊ አስተሳሰቦች (እንደ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የጥፋት ውሃ) እና የትኛው ምንጭ የበለጠ ታማኝ ነው ብለው ያስባሉ። ግምቶች በ20ኛው ክፍለ ዘመን በከፍተኛ ሁኔታ እየጠበቡ ነው፣ አብዛኛውም በ250 ዓመታት ውስጥ፣ በሦስተኛው ሺህ ዓመት ዓክልበ አጋማሽ አካባቢ ነው። አዲስ የተገነባው ራዲዮካርበን የፍቅር ግንኙነት ዘዴ ታሪካዊው የዘመን አቆጣጠር በግምት ትክክል መሆኑን አረጋግጧል። ነገር ግን በትላልቅ ህዳጎች ወይም ስህተቶች ፣ የመለኪያ ጥርጣሬዎች እና አብሮ የተሰራ የእድሜ ችግር (በዕድገት እና በመጨረሻው አጠቃቀም መካከል ያለው ጊዜ) እንጨትን ጨምሮ በእጽዋት ቁሳቁስ ምክንያት አሁንም ሙሉ በሙሉ አድናቆት ያለው ዘዴ አይደለም። ከግንባታው ጊዜ ጋር. የግብፅ የዘመን አቆጣጠር መጣራቱን ቀጥሏል እና ከበርካታ የትምህርት ዘርፎች የተገኙ መረጃዎች እንደ መጠናናት፣ ራዲዮካርበን መጠናናት እና ዴንድሮክሮኖሎጂ በመሳሰሉት ምክንያቶች መካተት ጀምረዋል። ለምሳሌ፣ . በሞዴላቸው ውስጥ ከ200 በላይ የራዲዮካርቦን ናሙናዎችን አካትቷል። የታሪክ መዝገብ የጥንት ግሪክ ታሪክ ጸሐፊ ሄሮዶተስ በ 5 ኛው ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት ሲጽፍ, ፒራሚዱን ከጠቀሱት የመጀመሪያዎቹ ዋና ደራሲዎች አንዱ ነው. በሁለተኛው መጽሃፉ ዘ ታሪክ ውስጥ፣ ስለ ግብፅ እና ስለ ታላቁ ፒራሚድ ታሪክ ይናገራል። ይህ ዘገባ የተፈጠረዉ አወቃቀሩ ከተሰራ ከ2000 አመታት በኋላ ነዉ ይህ ማለት ሄሮዶተስ እዉቀቱን ያገኘዉ በዋናነት ከተለያዩ የተዘዋዋሪ ምንጮች ማለትም ባለስልጣናቱን እና ቄሶችን ፣የሀገር ዉስጥ ግብፃዊያንን ፣የግሪክ ስደተኞችን እና ሄሮዶተስን እራሱ ተርጓሚዎችን ያጠቃልላል። በዚህ መሠረት የእሱ ገለጻዎች እራሳቸውን ለመረዳት የሚቻሉ መግለጫዎች, የግል መግለጫዎች, የተሳሳቱ ዘገባዎች እና ድንቅ አፈ ታሪኮች ድብልቅ ናቸው; ስለዚህም ስለ ሃውልቱ ብዙዎቹ ግምታዊ ስህተቶች እና ውዥንብሮች ከሄሮዶተስ እና ከስራው ሊገኙ ይችላሉ። ሄሮዶተስ ታላቁ ፒራሚድ የተገነባው በኩፉ (ሄለኒዝድ እንደ ቼፕስ) እንደሆነ ጽፏል እሱም በስህተት አስተላልፏል ከራምሲድ ዘመን (ስርወ መንግስት እና ) በኋላ ይገዛል። ክሁፉ አምባገነን ንጉስ ነበር ይላል ሄሮዶቱስ፣ እሱም የግሪኮችን አመለካከት እንደሚያብራራ እንዲህ ያሉ ሕንፃዎች ሊፈጠሩ የሚችሉት በሰዎች ላይ በጭካኔ በመበዝበዝ ብቻ ነው። ሄሮዶተስ በተጨማሪ እንደገለጸው 100,000 የጉልበት ሠራተኞችን ያቀፈ ቡድን በሦስት ወር ፈረቃ ውስጥ በሕንፃው ላይ ሲሠራ 20 ዓመታት ፈጅቷል። በመጀመሪያዎቹ አስር አመታት ውስጥ ሰፊ መንገድ ተዘርግቶ ነበር, ሄሮዶተስ እንደሚለው, የፒራሚዶቹን ግንባታ ያህል አስደናቂ ነበር. ወደ 1 ኪሎ ሜትር የሚጠጋ (0.62 ማይል) ርዝመት እና 20 ያርድ (18.3 ሜትር) ስፋት፣ እና ወደ 16 ያርድ (14.6 ሜትር) ከፍታ ያለው ሲሆን የተወለወለ እና በምስል የተቀረጸ ድንጋይ ነው። በተጨማሪም ፒራሚዶቹ በሚቆሙበት ኮረብታ ላይ የመሬት ውስጥ ክፍሎች ተሠርተዋል. እነዚህም የኩፉ መቃብር እንዲሆኑ የታሰቡ ሲሆን ከናይል ወንዝ በመጣ ቻናል በውሃ የተከበቡ ነበሩ። ሄሮዶተስ ከጊዜ በኋላ በካፍሬ ፒራሚድ (ከታላቁ ፒራሚድ አጠገብ በሚገኘው) አባይ ወደ ደሴት በተሰራ መተላለፊያ በኩል እንደሚፈስ ተናግሯል። ኩፉ የተቀበረበት። (ሀዋስ ይህንን ሲተረጉመው ከታላቁ ፒራሚድ በስተደቡብ በሚገኘው በካፍሬ መንገድ ላይ የሚገኘውን “ኦሳይረስ ዘንግ”ን ለማመልከት ነው።) በተጨማሪም ሄሮዶተስ ከፒራሚዱ ውጭ ያለውን ጽሑፍ ገልጿል፣ ተርጓሚዎቹ እንደሚሉት፣ ሠራተኞቹ በፒራሚዱ ላይ ሲሠሩ የሚበሉትን ራዲሽ፣ ነጭ ሽንኩርት እና ቀይ ሽንኩርት መጠን ያሳያል። ይህ የዳግማዊ ራምሴስ ልጅ ካምዌሴት ያከናወነው የተሃድሶ ሥራ ማስታወሻ ሊሆን ይችላል። በግልጽ ለማየት እንደሚቻለው የሄሮዶተስ ባልደረቦች እና ተርጓሚዎች የሂሮግሊፍ ጽሑፎችን ማንበብ አልቻሉም ወይም ሆን ብለው የተሳሳተ መረጃ ሰጡት። ዲዮዶረስ ሲኩለስ ከ60-56 ዓክልበ. መካከል፣ የጥንታዊው ግሪክ ታሪክ ጸሐፊ ዲዮዶረስ ሲኩለስ ግብፅን ጎበኘ እና በኋላም የእሱን የመጀመሪያውን መጽሐፍ ታላቁን ፒራሚድ ጨምሮ ለመሬቱ፣ ለታሪኳ እና ለሀውልቶቿ ሰጠ። የዲዮዶረስ ሥራ በጥንት ታሪክ ጸሐፊዎች ተመስጦ ነበር፣ነገር ግን ዲዮዶረስ አስደናቂ ተረቶችና አፈ ታሪኮችን ይናገራል ከሚለው ከሄሮዶተስ ራሱን አገለለ። ዲዮዶረስ እውቀቱን የሳበው ከጠፋው የአብደራው ሄካቴዎስ ስራ እንደሆነ ይገመታል እና እንደ ሄሮዶቱስ የፒራሚዱን ገንቢ "ኬሚስ"ንም ከራምሴስ 3ኛ ቀጥሎ አስቀምጧል። በሪፖርቱ መሠረት ኬሚስ (ኩፉ) ወይም ሴፍረን (ካፍሬ) በፒራሚዳቸው ውስጥ አልተቀበሩም ፣ ይልቁንም በሚስጥር ቦታዎች ፣ ግንባታዎችን ለመገንባት የተገደዱት ሰዎች ሬሳውን ለበቀል እንዳይፈልጉ በመፍራት ነበር ። በዚህ አባባል ዲዮዶረስ በፒራሚድ ግንባታ እና በባርነት መካከል ያለውን ግንኙነት አጠናከረ። እንደ ዲዮዶረስ ገለጻ፣ የፒራሚዱ ሽፋን በወቅቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ ነበር፣ የፒራሚዱ የላይኛው ክፍል ግን 6 ክንድ (3.1 ሜትር፣ 10.3 ጫማ) ከፍታ ባለው መድረክ ተሠርቷል። ስለ ፒራሚዱ ግንባታ እስካሁን ምንም አይነት የማንሳት መሳሪያዎች ስላልተፈጠሩ በመንገዶች ታግዞ መገንባቱን ይጠቅሳል። ፒራሚዶቹ ከተጠናቀቁ በኋላ እንደተወገዱ ከመንገዶቹ ምንም አልቀረም። ታላቁን ፒራሚድ ለማቆም የሚያስፈልጉትን ሰራተኞች ብዛት 360,000 እና የግንባታ ጊዜውን 20 አመት ገምቷል። ከሄሮዶቱስ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፣ ዲዮዶረስ ደግሞ ከፒራሚዱ ጎን “የአትክልትና ፍራፍሬ ዋጋ ለሠራተኞቹ ከአሥራ ስድስት መቶ መክሊት በላይ ተከፍሏል” በሚለው ጽሑፍ ተጽፎበታል ብሏል።
35745
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A9%E1%88%8B%E1%88%8A%E1%89%B5%20%E1%8C%A0%E1%8C%A0%E1%88%AD
የኩላሊት ጠጠር
የኩላሊት ጠጠር የሚባለው በኩላሊት ውስጥ የጠጣር ነገሮች መጋገር ወይም መሰብሰብ ሲሆን የጠጣር ነገሮቹም ምንጭ በሽንት ውስጥ የሚገኙ የምግብ ንጥረ ነገሮች ናቸው:: የኩላሊት ጠጠሮች ብተለያየ መልኩ ይከፋፈላሉ፣ ከነዚህም ውስጥ; በሚገኙበት ቦታ [በሽንት ትቦ ወይም ዩሬተር, በሽንት ፊኛ]; በጠጠሮቹ ውስጥ በሚገኙ ማእድናት [ካልሺየም የያዙ, ስትራቫይት (ማግኒዢየም, አሞኒየም ፎስፌት), የሸንት አሲድ ወይም ሌላ ማእድናት]:: የኩላሊት ጠጠር የህመም ምንጭ ሲሆን በአብዛኛው ወንዶችን ያጠቃል (፹ በመቶ . ወንዶች በአብዛኛው የኩላሊት ጠጠር ህመም ከ ፴ ባለው እድሜአቸው ሲጀምራቸው ሴቶች ላይ ግን ዘግይቶ ይከሰታል:: የኩላሊት ጠጠሮች በአመዛኙ ምንም የህመም ስሜትና ጉዳት ሳያስከትሉ በሽንት መስመር ውስጥ አልፈው ከሰውነት ይወገዳሉ:: ነገር ግን ጠጠሮቹ በመጠን ከጨመሩ ሚሜ አካባቢ ከደረሱ) የሽንት ትቦ ሊዘጉ ይችላሉ:: የሽንት ትቦ በጠጠር መዘጋት ሽንት በቀላሉ እንዳይተላለፍ (ፓስቴርናል አዞቶሚያ) ብሎም ሽንት ወደ ሁዋላ በመመለስና በኩላሊት ውስጥ በመከማቸት ጉዳት ሊያደርስ ይችላል (ሃይድሮኔፕሮሊስ):: ይሄ ችግር (ሃይድሮኔፕሮሊስ) ከታችኛው የጎድን አጥንት አንስቶ እስከ የዳሌ አጥንት (ሂፕ) ድረስ ባለው ቦታ, በብሽሽትና በታችኛው የምግብ መፍጫ ክፍሎች (ሎወር አብዶሜን) አካባቢ ለህመም ስሜት (ሬናል ኮሊክ) ይዳርጋል:: ሬናል ኮሊክ ከማቅለሽለሽና የማስታወክ ስሜቶች, ትኩሳት , በሽንት ውስጥ ደም መኖር በሽንት ውስጥ መግል የሚመስል ፈሰሽ (ፐስ) እና በሽንት ጊዜ ከከፍተኛ የህመም ስሜት ጋር ሊያያዝ ይችላል:: የሬናል ኮሊክ የህመም ስሜቶች በአመዛኙ ከ ፳ እስከ ፷ ደቂቃ በሚሆኑ ተመላላሽ የህመም ስሜቶች የታጀበ ሆኖ ከታችኛው የጎድን አጥንት ወይም ከታችኛው የጀርባ ክፍል ተነስቶ ወደ ብሽሽት ወይም የሽንት መሽኛ ብልቶች የሚሰራጭ የህመም ስሜት ነው:: የኩላሊት ጠጠር መኖር በሰውነት አቁዋም ምርመራዎች (በበሽታ ምልክቶች መኖር (ፊዚካል ኤግዛሚኔሽን)), በሽንት ምርመራ, በራጅ ምርመራ እንዲሁም በበሽተኛው የበፊት የጤና ምርመራ ውጤቶች ድጋፍ ይታወቃል:: የአልትራሳውንድ እና የደም ምርመራዎችም የኩላሊት ጠጠር በሽታ መኖሩን ለማወቅ አጋዥ ይሆናሉ:: የኩላሊት ጠጠር ህመም ካላስከተለ የሰውነትን ሁኔታ እየገመገሙ በጥንቃቄ መጠበቅ ጥሩ አማራጭ ነው:: ህመም ለሚያስከትል የኩላሊት ጠጠር በሽታ የመጀመሪያ እርዳታ ህመሙን መቆጣጠር መሆን አለበት:: ይሄም በ ነን ስቴሮዳይዳል አንቲ ኢንፍላማቶሪ ወይም አፒኦዲስ መድሃኒቶችን በመጠቀም ነው:: ከፍተኛ የሆነ የኩላሊት ጉዳት ወይም ህመም ከተከሰተ ግን የቀዶ ጥገና አስፈላጊ ሊሆን ይችላል:: ለምሳሌ, አንዳንድ ጠጠሮች በነዛሪ ሞገድ (ሾክ ዌቨ) አማካኝነት ወደ ጥቃቅን ጠጠሮች መሰባበር ሲቻል በአንዳንድ ሁኔታ ደግሞ የሰውነት መቀደድን ሊያስከትሉ የሚችሉ ቀዶ ጥገናዎች አስፈላጊ ሊሆን ይችላል:: አንዳንድ ጊዜም በሽንት መሽኛ ትቦ ውስጥ ሌላ ሰው ሰራሽ ትቦ (ዩሬትራል ስቴንት) በመቀጠል በጠጠር የተዘጋውን ቦታ ወደ ጎን አልፎ እንዲሄድና የህመም ስሜቱን መቀነስ ይቻላል:: የበሽታ ምልክቶች የሽንት ትቦና የሽንት ትቦ ከኩላሊት ጋር የሚገናኝበት ቦታ (ሬናል ፔልቪስን) የሚዘጋ የኩላሊት ጠጠር ልዩ ምልክት ከታችኛው የጎድን አጥንት እስከ ብሽሽትና የሽንት ብልት ድረስ የሚደርስ ከፍተኛ የሆነ ተመላላሽ የህመም ስሜት ነው። ይሄ ሬናል ኮሊክ ተብሎ የሚታወቅ ልዩ የህመም ስሜት ሃይለኛ ተብለው ከሚታወቁ የህመም ስሜቶች የሚመደብ ነው። በኩላሊት ጠጠር የሚከሰት ሬናል ኮሊክ ሽንት ቶሎ ቶሎ መምጣትን፣ የድካም ስሜትን፣ በሽንት ውስጥ ደም መኖርን፥ ማላብን፣ ማቅለሽለሽና ማሥታወክን ሊያስከትል ይችላል። የህመም ሥሜቱም ተመላላሽ በሆነና ከ ፳ ደቂቃ ሲቆይ ህመሙም የሽንት ትቦ ጡንቻ ጠጠሮቹን ለማስውገድ በሚያደርገው የመኮማትርና የመፍታታት እንቅስቃሴዎች (ፐሪስታልቲክ) የሚከሠሰት ነው። በፅንስ መጠንሠስ ጊዜ በሚከሰት የሽንት መተላለፊያ፤ የሽንት መሽኛ ብልቶችና፤ የምግብ ትቦዎች (ጨጉዋራ፣አንጀት) የተፈጥሮ ግንኙነት ምክንያት የኩላሊት ጠጠር በሽንት ብልቶች ላይ ህመም ከማስከተሉም በላይ ለማቅለሽለሽና ለማስታወክም ይህ የተፈጥሮ ቁርኝት መንስኤ ነው። ፖስተርናል አዞቶሚያ እና ሃይድሮሄፕሮሊስ (ትርጉም ከላይ) በአንዱ ወይም በሁለቱ የሽንት ትቦዎች መዘጋት ምክንያት ይከሠታል። ለኩላሊት ጠጠር መፈጠር ምክንያት ሊሆኑ ከሚችሉ የአመጋገብ ልምዶች መካከል፤ ውሃ በበቂ አለመጠጣት፣ ከፍተኛ የሆነ የእንሥሳት ሥጋ (ፕሮቲን) መመገብ፣ ጨው (ሶዲየም)፣ የተጣሩ ስኳሮች፣ የፍራፍሬ ስኳር (ፍሩክቶስ)፣ ኦክሳሌት የያዙ ምግቦች (ኦክሳሌት በብዙ ዕፅዋት ውሥጥ የሚገኝ ንጥረ ነገር ሲሆን በተለይም በሰባ ዶሮ፣ በጥቀር አዝሙድ??? (ብላክ ፒፐር)፣ ፐርስሊ፣ ስፒናች፣ ካካዎ፣ ቸኮላት፣ ኦቾሎኒ፣ አብዛኛዎቹ እንጆሬዎች ውስጥ ይገኛል)፣ የአፕል ጭማቂ እና የኮላ መጠጦች ናቸው። የመከላከያ መንገዶች የኩላሊት ጠጠርን ለመከላከል የሚደረጉ ጥረቶች በታማሚው ውስጥ በሚገኘው የኩላሊት ጠጠር አይነት (የማዕድን ይዘት) ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት። የአመጋገብ ሥልት በኩላሊት ጠጠር መፈጠር (መከማቸት) ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያደርግ ይችላል። የኩላሊት ጠጠርን መፈጠርን መከላከል (መቀነስ) የሚቻለው የአመጋገብ ሥልትን በማስተካከልና በሽንት ውስጥ የሚገኙ ለኩላሊት ጠጠር መከማቸት መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ የማእድናትን መጠን ለመቀነስ የሚረዱ መድሃኒቶችን በመጠቀም ነው። የህክምና ባለሙያዎች የሚከተሉትን የአመጋገብ ሥልቶችን መከተል የኩላሊት ጠጠርን ለመቀነስ እንደሚረዳ ያመለክታሉ፤ ሲትሬት (በሎሚና በብርቱካን ውስጥ የሚገኝ አሲድ ነው) ያላቸውን ፈሳሾች በብዛት መጠጣት፣ የፈሳሽ አወሣሠዱም በብዛትና በቀን እስከ ሁለት ሊትር የሽንት መጠን እሰኪደርስ ቢሆን ይመከራል። በዚህ መንገድ የሽንትን ፒኤች 6.5 አካባቢ በማድረግ በተለይ በሽንት አሲድ (ዩሪክ አሲድ) ምክንያት የሚመጡ ጠጠሮችን ለማስወገድ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያደርጋል። የካልሺየም አወሳሰድ መጠንን ከ 1000-1200 ሚግ መጠን በቀን ውስጥ ከፍ ማድረግ የሶዲየም አወሳሰድ መጠንን ከ 2300 ሚግ በቀን በታች እንዲሆን ማድረግ የቪታሚን ሲ የቀን ፍጆታን ከ 1000 ሚግ በቀን በታች እንዲሆን ማድረግ የእንሥሣት ፕሮቲን (ስጋና ሥብን) ከሁለት ጊዜ በታች ማድረግና መጠኑንም ከ 170-230 ግራም እንዳያልፍ መቆጣጠር እና ኦክሳሌት የያዙ ምግቦችን (ከላይ ተጠቅሰዋል) መቀነስ ናቸው።
50396
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8B%8A%20%E1%89%A5%E1%88%84%E1%88%A8%E1%88%B0%E1%89%A5%20%E1%8B%9E%E1%8A%95
አዊ ብሄረሰብ ዞን
አዊ ዞን ➡ የዞኑ ዋና ከተማ፡- እንጅባራ ➡ የዞኑ ዋና ከተማ ከክልሉ ዋና ከተማ ያለው ርቀት-122 ኪ.ሜ ➡ የወረዳዎች ብዛት፡- 9 አንካሻ ጓጉሣ ባንጃ ሽኩዳድ ጓጉሣ ሽኩዳድ ፋግታ ለኮማ ዳንግላ ወረዳ ጃዊ ወረዳ ጓንጓ ወረዳ ዚገም ወረዳ አዘና ወረዳ ➡ የከተማ አስተዳደሮች ብዛት፡- 5 አዲስ ቅዳም ➡ የቀበሌዎች ብዛት፡-201 የከተማ፡- 23 ➡ በዞኑ ውስጥ የሚገኝ ህዝብ ብዛት፡-1,058,289 ➡ የወረዳው ስም የወረዳው ዋና ከተማ አንካሻ ጓጉሣ - አገው ግምጃ ቤት ባንጃ ሽኩዳድ - እንጅባራ ጓጉሣ ሽኩዳድ - ቲሊሊ ፋግታ ለኮማ - አዲስ ቅዳም ዳንግላ ወረዳ - ዳንግላ ጃዊ ወረዳ - ፈንድቃ ጓንጓ ወረዳ - ቻግኒ ዚገም ወረዳ - ቅላጅ አዘና/አዮ ወረዳ - አዘና የአገው ሕዝብ አሁን በሚገኝባቸው የተለያዩ አካባቢዎች ራሱን የሚገልጸው አዊ ፡ኽምራ፡ቅማንት ፡ብሊን በሚሉ አካባቢያዊ መጠሪያዎች ነው ! የስያሜው እድገት ከራሳቸው ወይም በጋራ ከሚገኝ ማህበረሰብ ክፍሎች ተጨማሪ ቋንቋ የተዋሱት ነው ✓አዊ ማለት አገው ማለት ነው ፡የቃሉ መነሻና ምንጭ የራሱ ቋንቋ አገውኛ ነው ሌሎችንም ራሱንም አገው ለማለት ና ለመግለጽ ይህንኑ ቃል ይጠቀማል። ✓ ኽምራ ማለት አገው ማለት ነው የቃሉ መነሻና ምንጭ የራሱ ቋንቋ አገውኛ ነው ፡ሌሎቹንም ራሱንም አገው ለማለት ይኸንኑ ቃል ይጠቀማል። ✓ቅማንት ማለት የቤተሰብ ውቅር አሰያየም ወይም የባሕላዊ ሃይማኖት ማህበረሰባዊ ልየታ ሲሆን የቃሉ መነሻና ምንጭ አማርኛ ነው ፡ ቃሉን የሚጠቀሙት የኦርቶዶክስ ክርስትያን ተከታዬች ሲሆኑ ክርስትናም ይሁን ይሁዲ እምነት የማይከተሉትን ቀደምት አገዎችን ክርስትያን አማሮች የሚገልጹበት ስያሜ ነው ። ✓ብሊን ማለት አገው ማለት ነው ፡የቃሉ መነሻና ምንጭ የራሱ አገውኛ ቋንቋ፡የቤላ ትውፊትና በጋራ ካሉት የሳሆ ቋንቋ ተናጋሪዎች የተወሰደ ሲሆን አገዎች ራሳቸውንና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ደግሞ አገዎችን ለመግለጽ ይጠቀሙበታል። የአገው ታሪክ እማዱክ ታሪክ አገው ምድር (አዊ ላጜታ) በሀገሪቱ ስርዓት አዊ ብሄ/አሰ/ዞን እየተባለ የሚጠራው አካባቢ ሰው ያልነበረበት ፣ጥቅጥቅ ያለ ጫካ በዱር አራዊት የተሞላ ፣ ንፁህ የአየር ንብረት ለም አፈር ፣በቂ ውሃ ምቹ መልካአ ምድራዊ አቀማመጥ፣ የጫካ ማር ያለበት ጠፍ እንደነበረ አፋአዊ መረጃዎች ይጠቁማሉ ፡፡ ይሁን እንጂ የዚህ ቦታ ስያሜ የተሠጠው በአካባቢው በቀዳሚነት በሰፈሩት ሰባቱ አገው ወንድማማቾች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ አገው ምድር እየተባለ የሚጠራው ቦታ በመጀመሪያዎቹ ነዋሪዎች ሲሰየም ክልሉ (ወስኑ እስከ የት እንደነበር በትክክል መግለፅ ባይቻልም ከአሁኑ አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ስር ካሉ ወረዳዎች በላይ እንደነበር እንዲሁም በምስራቅ ጎጃምና ደ/ጎንደር አካባቢ በአዊኛ ቋንቋ የሚጠሩ አካባቢዎች (ቦታዎች )መኖራቸው ለብሄ/አስ/ዞን ወስንና ስፋት ዋነኛ እማኞች ለምሳሌ፡- ድኩል ካን ፣ዳድ ዩሃንስ (ምስ/ጎጃም ) ቢዝራ ካኒ (ጎንደር) ፃና (ጣና) የሚባሉት ተጠቃሽ ናቸው ሰባት ቤት አገው (ላጜታ አዊ) የተጠናከረና የተደራጀ መረጀ ባይኖርም በአፈ ታሪክ ደረጃ ከተለያዩ አባቶችና ታሪክ አዋቂዎች የተገኙ መረጃዎች ( እንደሚጠቁመን የእስራኤል ደም ወገን የሆነው ንጉስ ሰለሞን የልጅ ኩሳ ከቀዳማዊ ሚኒሊክ ጋር ታቦተ ፅዮንን ከእየሩሳሌም ይዘው ከመጡ በኋላ ንጉስ ኩሳ ሰቆጣ አካባቢ ትዳር መስርቶ በመኖር አዲልን ወለዱ ፣አዲል ደግሞ እና አንከሻ፣ባጃ፣መተከል፣አዘ ና፣ዚገም፣ኳኩራና ጫራን ወለዱ እነዚህ ወንድማማቾች ከአካባቢያቸው ወደ ተለያዩ ቦታ እየተዘዋወሩ ዱር አራዊትን በማደን አዘውትረው ሲኖሩ ኑሮን ለማሸነፍ ፣ህይወትን በተሻለ መንገድ ለመምራት ከተፈጥሮና አካባቢ ጋር መታገል ግድ ይላል ፡፡ ካልሆነም አካባቢን ለቆ የተሻለ አካባቢ ፍለጋ መኳተን አሁንም በአንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋል ተግባር ነው ፡፡ ስለሆነም ስባቱ አገዎች በአንድ ተሰማርተው በወቅቱ ውድና ተፈላጊ የሆኑ የዱር አራዊት ማለትም የዝሆን ጥርስ ፣ጥርኝ ፣ዝባድና የመሳሰሉትን ፍለጋ ሲጓዙ የትውልድ ቦታቸውን ስቆጣ ለቀው አሁን እንጅባራ እየተባለ ወደ ሚጠራው አካባቢ (ከሰንግ ይባል )ነበር ደርሰው አሁንም በአዊኛ “አንጉች ካና” ይባላል ፡፡ አካባቢው ምንም ሰው የሌለበት ፣በቂ የሆነ የዱር አራዊትና ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ፣የዱር ማር ያለበት ፣ምቹ መልካዓ ምድራዊ አቀማመጥና ሰላም የሰፈነበት ቦታ ሆኖ በማግኘታቸው በአካባው ሁኔታና ተፈጥሮአዊ አቀማመጥ በመማረክ ለሰባት ወራት ያህል የዱር አራዊትን በማደን ቆይተው ሰባቱም ወንድማማቾች ወደ ቤተሰቦቻቸው (ሰቆጣ ) በመመለስ፣ለቤተሰቦቻቸውም ተመላልሰው ስለተመለከቱት አካባቢ መልካዓ ምድራዊ አቀማመጥ ፣ለኑሮ ምቹና ተስማሚ የአየር ንብረት ፣በውስጡ ያሉ የዱር አራዊትና ተፈጥሮአዊ ገፅታ ሲገልፁላቸው ቤተሰቦቻቸውም በሀሳባቸው ተስማምተው ለጥያቄአቸው አወንታዊ ምላሽ በመስጠት መልካም ፈቃዳቸውን መርቀው ልጡን ገመድ፣ባዳውን ዘመድ ያድርላችሁ ሲሉ ሰባቱ ወንድማማቾች ሚስቶቻቸውን ልጆቻቸውን ከብቶቻቸውን እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው አገልጋያቸው ትሆን ዘንድ የተላከቸውን አዱክን ጨምረው ጎዞቸውን ወደ ተመለከቱት አካባቢ ቀጠሉ፡፡ ወደ አዲሱ አካባቢ ደርሰው በታላቃቸው አንከሻ መሪነት ቦታ ሲከፋፈሉ አንከሻና ባንጃ አማካኝ የሆነ ቦታ ሲይዙ ኳክራን በምስራቅ ፣ጫራን በምዕራብ፣ዚገም፣መተከልና አዘና በስተደቡብ እንዲቀመጡ አድርገዋል፡፡ አማካይ በሆነ አቅጣጫ አንከሻና ባንጃ በመሆን አዱክ ታገለግላቸው ነበር ፡፡ በተጨማሪም ለሌሎች ወንድማማቾች በመሆኑ እንደ መገናኛ ይጠቀሙበት ነበር ይላሉ የታሪክ አባቶች ፡፡ አዱክ ከሰባቱ ወንድማማቾች ጋር በአገልጋይነት ከሰቆጣ የተላከችው አዱክ ስትቅልባቸውና ስታገለግላቸው ኑራ አምስቱ በተልያዩ አቅጣጫ ቦታ ቦታቸውን ሲይዙ እሷ ግን በታላቃቸው አንከሻና ባንጃ መካከል በመሆን እንድትኖር ተደርጓል፡፡ በመሆኑም አገልጋያቸው አዱክ በዕድሜ እየገፋች ለስራ ጉልበቷ እየደከመ ሲሄድ እንደገና መጦር ግድ ሆነባት ፡፡ በሁለቱ ወንድማማቾች ትርዳና ትጦር ጀመር ይህም ሲሆን አንከሻ በደቡብ አብልቶ አጠጥቶ አጥቦና አልብሶ ድንበራቸው በሆነ ቦታ ላይ ፀሐይ ሲሞቅ ብርዱም ሲለቅ አስቀምጦ ሲሄድ ፣ባንጃም በተራው በመውሰድ ቤቱ አሰንብቶ ለተረኛው ሲሰጥ እንደቤቱ አብልቶና አጠጥቶ በጥዋቱ ፀሐይ ሰትታይ ከቦተዉ የደርሣት ነበር በመሆኑም አዱክ በጥዋቱ ቁርና በቀጥር ሙቀት ይፈራረቀባት ስለነበር አንከሻንና ባንጃን ትመርቃቸው ነበር ይላሉ አባቶች(አባሆይ ዘሩ አለሙ) አንከሻን /ክምምባ ኹ ክም አንካ እይምኽ /እስከ ማታ ብላ ባንጃን ስግላ ቻንቑዋ ስግላ አንካ ኹ /የማለዳ እንጀራ ብላ/ እማ አዱክ የተለያዩ መላምቶች “አዱክ” የሰባቱ አገው እናት ናት እየተባለ ሲወራ ይስተዋላል ፡፡ ስለሆነም ከተለያዩ አባቶች ታሪክ አዋቂዎችና የአካባቢ ነዋሪዎች የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው አዱክ የሰባቱ አገው ወንድማማቾች “ ወላጅ እናት ” አይደለችም ነገር ግን እነሱ ወደ ዚህ አካባቢ ሲመጡ ከቤተሰቦቻቸው የተላከች አገልጋያቸው (ሞግዚታቸው ናት ) የሰባቱ ወንድማማቾች እናት ማናት ? ሲባል አዱክ ይባላል ይህም የሆነበት ምክንያት 1. የብረሄረሰቡ ባህል ፣ ቋንቋና ወግ መሰረት በዕድሜ ትልቅ የሆነች እህት ፣አክስት ፣የእንጀራ እናት ወይም አሳዳጊ 2. በኢትዮጴያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት መሰረት የክርስትና እናት 3. በመኳንት ወይም መሳፍንት ቤተሰብ ቤት ውስጥ የምታገለግል ፣ሴት የልጅ ጠባቂ ፣ቀላቢ እና ተንከባካቢ እንደ ወላጅ እናት “እናት” ተብላ እንደምትጠራ ይታወቃል ፡፡ ስለሆነም አዱክ የሰባቱ አዊ እናታቸው ሳትሆን ቀላቢያቸውና አገልጋያቸው እንዲሁም የልጆቻቸው ሞግዚታቸው በመሆኗ እናት ተብላ ትጠራለች ፡፡ አዱክ በአንዳንድ አካባቢዎች እማ-አዱክ ተብሎ ስሟ ሲጠራ ይስተዋላል፡፡ ይህ የሆነው “እማ” የሚለው ቅፅል ስም በዕድሜ ትልቅ ለሆኑ ሴቶችና እናቶች የሚሰጥ የክብር ስም በመሆኑ አዱክ የሰባት አገዋች አገልጋያቸውና የልጆቻቸው ሞግዚትም ስለሆነች እማ አዱክ እየተባለች በክብር ስትጠራ፣(በማ/ሰቡ ባህል ፣ወግ፣ቋንቋ የእምነት ስርዓት መሰረት ፣ታላቆችን በስም ብቻ አይጠሩም ፣በአክብሮት፣በትህትናና በማዕረግ ስማቸው ይጠራሉ። የአዱክ መቃብር በኳሪ ጎኻና ቀበሌ ፣በተርዬ ታራረ ዙሪያው በጥድ ዛፍ የተከበበ ካችንቲ ተራራ (አለት በስተ ደቡብ ፣የእማ አዱክ መቃብር ስፍራ ይገኛል፡፡ ምክንያቱም የድንጋይ ቁልል ይታያል፡፡ የመቃብር ቦታ እዚህ ለመሆኑ የሚያመለክቱ መረጃዎች 1. እማ አዱክን አንከሻና ባንጃ ይጦሯት ስለነበረና ይህ ቦታ ደግሞ የሁለቱ ወሰን (ድንበር መሆኑ ) 2. አንከሻና ባንጃ በሚጦሯት ጊዜ የሚረካከቡበት ቦታ ስለነበር 3. ይህ ቦታ ለሰባቱም ወንድማማቾች አማካይ (መገናኛ) በመሆኑ በታላቆች ምክርና መሪነት መመሪያቸው 4. በወቅቱ በቅርብ ርቀት (አካባቢ ቤተ ቤተክርስቲያን አለመኖር ተጠቃሽ አፋዊ መረጃዎች ናቸው ፡፡ በሰሜን የባንጃ በአሁኑ ወረዳችን ፋግታ ለኮማ ፣በስተ ደቡብ የአንከሻ (በሁኑ ባንጃ ወረዳ ) ክልል ፣ከአ/ቅዳም ከተማ ወደ ኮሰበር በሚወስደው ------መንገድ ፣አሮጌ እንጅባራ ወይም በድሮ አጠራር ሰፈር ገቢያ እንዳደረስን ወደ ቀኝ በኩል በመታጠፍ ቀጥ ብለን ብንሄድ በግራና በቀኝ በጥድ ዛፍ የተከበበ ልዩና ማራኪ የሆነ ታሪካዊ ቦታን እናገኛለን፡፡ ይህ ቦታ - በቀደምት አዱክን አንከሻና ባንጃ የሚረካከቡበት ሲሆን - ዙሮ ዙሮ ቤት ፣ኑሮ ኑሮ ሞት እንዳሉ በኋላም የእማዱክ መቃብር ስፍራ ነው ፡፡ እዚህ ቦታ መሀል ለመሀል ሰፊ የሆነ ጎዳ/መንገድ ከአ/ቅዳም ና እንጅባራ ወደ ኳሪ ጎኻና የሚያደርስ ሲኖረው በዚህ መንገድ የሚያልፍ ማንኛውም ሰው እንደሌለው አካባቢ ምንገድ አቋርጦ አያልፍም / አይሄድም ልዩ የሆነ ባህላዊ ታሪካዊ ስርዓት ያለማንም መካሪነትና ትዕዛዝ ሲፈፀም/ሲከናወን ይታያል፡፡ ይኸውም መንገደኛው እማዱክ መቃርብ ሊደርስ የተወሰነ ርቀት ሲቀረው በቀኝ እጁ ድንጋይ ይዞ መጣል አያያዙም እንደ ማንኛውም ተራ ውርወራ ሳይሆን ልክ በቀኝ እጁ ይዞ በትክሻው ቀጥታ ቦታው ላይ ሲደርስ በቀኝ በኩል ካለው የድንጋይ ክምር ይጠለዋል ፡፡ በመቀጠልም እዚች ቦታ ላይ ቁጭ ብሎ ያርፋል ፡፡ ይህ የሚካሄደው ምን ጊዜ በቀኝ በኩል ባለው ስፍራ ነው ፡፡ ለምን ቢሉ - በቀኝ እጅ መያዛቸው ቀኝ እጅ ሁልጊዜም ገር ፣ቀናና መልካም ዕድልና ምኞች በመሆኑ - ከቦታው ሲደርሱ ማረፊያ መቀመጫቸው ከእናታቸው በረከት - ድንጋይ መጣል እረም ማውጣት ለመቃብር መታሰቢያነት ይህም በማ/ሰብ ወግና ባህል መሰረት ሰው ሲሞት እልቅሶ ቦታ ላይ ሲደርሱ ፊት ይጠረጋል ፣ቁጭ ብለው መነሳት፣ለወደፊቱም ለነፍስ መልካም መመኘት የተለመደ ስርዓት ነው ፡፡ የተለያዩ የፅሑፍ መረጃዎችን አፋዊ መረጃዎችን በመጠቀም መረጃዎችን በመሰብስብ ፅሑፉን ማጠናከር ተችሏል ፡፡ ወረዳችን ይህንና የመሳሰሉ ጥንታዊና ታሪካዊ ህዝብ ባለቤት ልዩ ልዩ ጥንታዊና ባህላዊ ቅርሶች መገኛ የተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ መስህብ ስፍራዎች ባለቤት መሆኑን መገለጫ ለሆነው ባህላችንና ቅርሶቻችን ትኩረት ሰጥተን መጠበቅ መንከባከብና ተጠብቀው ለትውልድ የሚተላለፉበትን መንገድ ማመቻቸት የሁላችንም የህሊና ግዴታ ሊሆን ይገባናል ፡፡ የአገው ታሪክ የአገው ታሪክ እጅግ ሰፊ ነው፡፡ ባለታሪክ ህዝብ አሁን ሰዓት በአስተዳደር ችግር ወደ ልመነ ወጦዋል የላስታ _ ዋግ ( ዛጉዌ ) ነገስታት ስም ዝርዝርና የነገሱበት ዘመን 1. መራ ተክለ ሃይማኖት ...920 _ 933 አ.ም ...13 አመት 2. ስቡሀይ ( ድልነአድ )...933 _ 943 አ.ም ...10 አመት 3. መይራሪ ... 943 _ 958 አ.ም ...15 አመት 4. ሀርቦይ ( ሀረየነ እግዚእ ) ...958 _ 966 አ.ም ...8 አመት 5. መንግስትነ ይትባረክ...966 _ 973 አ.ም ...7 አመት 6. ይእቀብከ እግዚእ...973 _ 983 አ.ም...10 አመት 7. ዜና ጴጥሮስ ...983 _ 989 አ.ም...6 አመት 8. ባህር ሰፍ...989 _ 1003 አ.ም....14 አመት 9. ጠጠውድም ( ፀር አሰግድ )...1003 _ 1013 አ.ም ...10 10. ጃን ስዩም ( አኩቴት ) ...1013 _ 1033 አ.ም...20 አመት 11. በእምት ( ግርማ ስዩም )...1033 _ 1053 አ.ም ...20 አመት 12. ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ...1053 _ 1093 አ.ም...40 12. ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ...1053 _ 1093 አ.ም...40 አመት 13. ቅዱስ ገብረ ማርያም...1093 _ 1133 አ.ም...40 አመት 14. ቅዱስ ላሊበላ...1133 _ 1173 አ.ም...40 15. ነአኩቶ ለአብ ...1173 _ 1213 አ.ም...40 አመት 16. ይትባረክ ... 1213 _ 1253 አ.ም...40 አመት የነገሱበት አመት ድምር 333 ይሆናል። @ ምንጭ # የአገው ህዝቦች ና የዛጉዌ ስርወ መንግስት ታሪክ በ ዶ/ ር አያሌው ሲሳይ @ ከገፅ 92 የተወሰደ።
52715
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%88%E1%88%8B%E1%8B%AD%E1%89%B3%20%E1%8B%98%E1%88%98%E1%8A%95%20%E1%8A%A0%E1%89%86%E1%8C%A3%E1%8C%A0%E1%88%AD
የወላይታ ዘመን አቆጣጠር
ስለ ጊፋታ በዓል አከባበር አጭር ማብራሪያ [በደስታ ወጋሶ የጊፋታ በዓል ምንነት የወላይታ ብሔር የበርካታ የማይዳሰሱ ቅርሶች ባለቤት ነው፡፡ ከእነዚህ ሀብቶች መካከል የብሔሩ ዘመን መለወጫ በዓል ጊፋታ አንዱ ነው፡፡ ጊፋታ የወላይታ ሕዝብ በኦሞ ወንዝ ተፋሰስ ቋሚ ኑሮ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ሲተገብሩት የቆዬ ከማንኛውም ባህላዊ እምነትም ሆነ ዘመናዊ ኃይማኖትና የአምልኮ ሥርዓት ጋር ምንም ግኑኝነት የሌለው የዘመን መለወጫ ክብረ በዓል ነው፡፡ የጊፋታ በዓል ትርጉም እንደ ብሔሩ የታሪክ አዋቂ ሽማግሌዎች ጊፋታ በብሄሩ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ታላቅ በዓል ሲሆን ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ የብሔሩ ማንነት መገለጫ የሆነ የአሮጌው ዓመት ማብቅያና የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ የመሸጋገሪያ በዓል ነው፡፡ ጊፋታ ማለት ባይራ(ታላቅ)፣ መጀመሪያ እንደ ማለት ሲሆን በሌላ በኩል ጊፋታ ማለት መሻገር ማለት ነው፡፡ ይህም ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሻገር የሚለውን ይገልጻል፡፡ ጊፋታ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ አእዋፋትና የቤት እንስሳትም ጭምር በጋራ የሚያከብሩት በዓል ነው ተብሎ ይታመናል፡፡ የወላይታ ብሔር የራሱ የሆነ የዘመን መቁጠሪያ/ካሌንደር አለው፡፡ በወላይታ የዘመን አቆጣጠር ጊፋታ የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ስያሜ ነው፡፡ በበዓሉ “” ተብሎ ይዘፈናል፡፡ ይህም የበዓሉን ታላቅነት ለመግለጽ ነው፡፡ የዘመን አቆጣጠር፡- አሮጌው ዓመት እየተገባደ ሲሄድ በንጉሱ አማካሪዎች አማካይነት የዘመን ቆጠራ ባለሙያዎች ወደ ቤተመንግሥት ይጠራሉ፡፡ ከዚያም ሌሊት ሌሊት እየወጡ የጨረቃን ኡደት መነሻ ለማወቅ የጨረቃን አራት ክፍሎች ማለትም /ፖኡዋ፣ ጡማ፣ ጤሯ፣ ጎባና/ በየትኛው ክፍል እንደሚውል የዓመቱን የቆጠራ ምልክቶች ይዘው መጥተው የሙሉ ጨረቃዋን ኡደት ተመልክተው ለንጉሱና ለአማካሪዎቹ ያበስራሉ፡፡ ከዚያም ኮከብ ቆጣሪዎቹ በዓሉ የሚከበርበት ቀን በትክክል ለንጉሱ ከነገሩ በኋላ ሽልማት ይዘው ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ፡፡ ቀጥሎም ንጉሱ የበዓሉን መቃረብ ለህዝቡ “በጫላ ኦዱዋ” (አዋጇ) በየገበያውና የህዝብ መሰብሰቢያ እንዲነገር ያደርጋል፡፡ የጊፋታ በዓል ታሪካዊ አመጣጥ የጊፋታ በዓል ታሪካዊ አመጣጡን በተመለከተ በዘመናዊ ታሪክ አቆጣጠር ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ በአካባቢው ይከበር የነበረ በዓል እንደሆነ ይገመታል፡፡ ነገር ግን በዓሉ መቼና እንዴት ተጀምሮ እያደገ እንደመጣ ትክክለኛውን ጊዜ የሚጠቁም መረጃ በብዛት ባይኖርም ለበዓሉ ታሪካዊ አመጣጥ ሁለት ዋና ዋና አመለካከቶች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ የመጀመሪያው አመለካከት በወላይታ መንግሥት ተመስርቶ ግዛቱን ተቆጣጥሮ መኖር ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ማለትም የመጀመሪያው የወላይታ ማላ ዘረ-ግንድ ቀዳሚ ንጉስ “ካዎ ቢቶ” ዘመነ መንግስት ጀምሮ ሲከበር እንደነበርና ይህንንም ከአያት ቅድመ-አያት “” መሠረት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ነው ተብሎ በአፈ-ታሪክ ይነገራል፡፡ ሁለተኛው አመለካከት ደግሞ “በሞቼና ቦራጎ” ዋሻ እየተደረገ ካለው የአርኪዮሎጂ ጥናት ውጤት ጋር የተያያዘ ሲሆን መረዳት የሚቻለው ሴኖዞይክ ኤራ (የድንጋይ ወይም የበረዶ ዘመን) በመባል ስለሚታወቀው ዘመን በዓለም ላይ ምርምር ከሚካሔድባቸው ሰባት ታላላቅ የምርምር ቦታዎች አንዱ በሆነው በዚህ ዋሻ ከ58,000 እስከ 70,000 ዓመት በፊት የወላይታ ሕዝብ ሆነ ሌሎች የአካባቢው ህዝቦች በዚህ አካባቢ የተረጋጋ(ቋሚ) ሕይወት የጀመሩበት ጊዜ መሆኑን የፕሮፌሰር ስቴቨን 4ኛ ዙር ጥናት ግኝት ሪፖርት ያመለከታል፡፡ ይህ ጥናት ፍንጭ የሚሰጥ ምልክት የተገኘበት ለቀጣይ ጥናት ሁኔታ የሚመቻችበት ብለው መዝግበው አቆይተዋል፡፡ የበዓሉ አከባበር ጅማሮም ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡ እነዚህን ሁለት መላምቶችን መነሻ አድርገን በምናይበት ጊዜ የመጀመሪያው የጊፋታን በዓል አጀማመር ከወላይታ ቋሚ መንግስት መመሥረት ጋር ያገናኛል፡፡ ሆኖም ግን ሰዎች በአንድ አካባቢ ተሰባስበው በዓላትን ለማክበር የግድ መንግሥት በሚባል የአስተዳደር መሣሪያ ሥር መሆን ያለባቸው አይመስለንም፡፡ ምክንያቱም በቀደሙት ጊዜያት በአካባቢያችን የሚገኙ የተለያዩ ብሄሮችና ብሔረሰቦች ራሳቸውን የሚያስተዳሩበት የተደራጀ መንግሥታዊ መዋቅር ባይኖራቸውም የተለያዩ ሕዝባዊ በዓላትን ያከብሩ እንደነበር ታሪካቸው ያስረዳል፡፡ በእኛ እምነት በአንድ አካባቢ ሰዎች ቋሚ ኑሮ መኖር ሲጀምሩ ማህበራዊ ግንኙነታቸው እየሰፋና እየተጠናከረ ይሄዳል፡፡ በዚህን ጊዜ የአምልኮ ሥርዓት፣ የሐዘንና የደስታ አገላለጽ፣ የበዓላት አከባበርም ጭምር በማህበር/በህብረት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ ስለሆነም የወላይታ ሕዝብ የዘመን መለወጫ በዓሉን ማክበር የጀመረው በንጉስ መተዳደር ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ሳይሆን በኦሞ ወንዝ ሸለቆ ቋሚ ኑሮ መኖር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ነው የሚለው መላምት የተሻለ ሳይንሳዊ አገላለጽ ያለው መሆኑን እናምናለን፡፡ የጊፋታ በዓል ቅድመ ዝግጅት፡- የጊፋታ በዓል ከሌሎች በዓላት በተለየ የረዥም ወቅት ዝግጅት ይደረግለታል፡፡ ሁሉም የማህበረሰቡ አባላት ማለትም አባቶች፣ እናቶች እንዲሁም ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሕጻናትም ሳይቀሩ በጊፋታ በዓል ዝግጅት የየራሳቸው የሥራ ድርሻ አላቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቅድመ ዝግጅት ሥራው በማህበር ወይም በደቦ ሆኖ አንዱ ሌላውን በማገዝም ይከናወናል፡፡ በጊፋታ ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻ አላቸው፡፡ የአባወራዎች ተግባር የጊፋታ በዓል ዝግጅት የሚጀምረው በቁጠባ/”ቆራጱዋ” ነው፡፡ ይህም በጊፋታ ዕለት ወንዶች በሬ ከታረደ በኋላ ከሁሉም የሥጋ ዓይነት ከየዓይነቱ ትንሽ ትንሽ ቆርጠው በባለተራው ቤት በተዘጋጀው ማባያ ማለትም ቆጮ፣ ቂጣ፣ ዳታ በርበሬ ጋር የ”አሙዋ” አባላት በጋራ ይቋደሳሉ፡፡ ይህም የአንድነትና የፍቅር ማብሰሪያ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ከዚያም የተከፋፈሉትን ሥጋ ከመውሰዳቸው በፊት ለመጪው ዓመት በሬ መግዣ አሁን በታረደው በሬ ቆዳ ላይ ተቀማጭ ገንዘብ ማሰባሰብ ይጀምራሉ፡፡ ይህንንም ስርዓት የጋዚያ ጨዋታ ሲጠናቀቅ በየሳምንቱ ገንዘቡን በታማኝ አባወራ ቤት ቁጠባውን ይቀጥላሉ፡፡ በመጨረሻም ዓመቱ ሲጠናቀቅ ተሰብስበው በሬ ከገዙ በኋላ የሚተርፈውን ገንዘብ ለቤት ውስጥ ወጪ ይጠቀማሉ፡፡ ለምግብነት የሚውሉ የምግብ ዓይነቶችን በዘር ወቅት መዝራት መሰብሰብና ለጊፋታ ወቅት ለይቶ ማስቀመጥ፤ ከበዓሉ ቀደም ብሎ ለማገዶ የሚሆኑ እንጨቶችን ሰብስቦ(ፈልጦ) ማከማቸት፤ በጊፋታ ወቅት ለከብቶች የሚሆን ሳር በበቂ ደረጃ አጭዶ መከመር፤ በዓሉ ሲቃረብ ለልጆች አዳዲስ ልብሶችን መግዛት፤ ለቅመማ ቅመም መግዣ የሚሆን ገንዘብ ለእናቶች መስጠት የመሳሰሉት ናቸው፡፡ ከዚህም ሌላ ከአባዎራዎች ተግባር አንዱና ዋንኛው የበሬ ግዥ ነው፡፡ ለጊፋታ የሚታረድ በሬ ለመግዛት ሲፈለግ ከአሙዋ አባላት መካከል ሦስት ሰዎች ተመርጠው በገንዘብ ያዡ ቤት የጧት ቡና ከጠጡ በኋላ ገንዘብ ያዡን ይዘው ወደ ገበያ ይሄዳሉ፡፡ ገበያ እንደደረሱም ቢቀለብ በአጭር ጊዜ ሊሰባ የሚችል በሬ ዋጋ ተደራድረው ገዝተውና በአዲስ ገመድ አስረው በልጆች በማስጎተት ወደ “አሪያዋ” ቤት ያመጣሉ፡፡ “አሪያዋ“ ማለት በሬውን እስከ እርድ ዕሁድ ዕለት ድረስ በቤቱ አስሮ የሚንንከባከብ ተረኛ የ“አሙዋ “ አባል ማለት ነው፡፡ ለእርድ ቀን ከሁለት ወር በላይ የሚሆን ጊዜ ሲቀረው የተገዛው በሬ ለ”አርያዋ” ይሰጣል፡፡ ለበሬው ምቹ ቦታ ቀድሞ በዚህ ቤት እንዲዘጋጅ ይደረጋል፡፡ የጊፋታ በሬ እንደሙሽራ ስለሚታይ ሰው እንዳያየው የተለየ ጋጣ ተዘጋጅቶ ሁሉም ቀዳዳዎች በቆናሽያ (በደረቅ የኮባ ቅጠል) ከምግብ መስጫ ጠባብ በር ውጪ ሙሉ በሙሉ ይሸፈናል፡፡ ከዚያም የአሙዋ አባለት ስኳር ድንች፣ የበቆሎ አገዳ፣ በቆሎ… በልጆቻቸው እያሸከሙ ወይም በአህያ እየጫኑ በየተራ በማምጣጥ ይቀልባሉ፡፡ ቀጥሎም በየ15 ቀኑ ተሰብስበው በሬውን ወደ ውጪ በማውጣት ያለበትን ደረጃ በማየት በጣም እየወፈረ ከሆነ ተንከባካቢውን እያሞገሱ አስተያየት ይሰጣሉ፡፡ በዚህ ዓይነት የጊፋታ በሬ ይቀለባል፡፡ ሌላው በአባቶችና በወንድ ልጆቻቸው የሚከናወን የአካባቢ እድሳት ሥራ ነው፡፡ ይህም በወላይታ ብሔር አዲስ ዓመት የመታደስ ምልክት ስለሆነ ሰዎች በግላቸው የቤታቸውን የሳር ኪዳን በአዲስ ሳር መቀየር፣ በቤት ውስጥ ያረጁትን ነገሮች ማለትም ቃረጣ፣ ቁሩጧ፣ ሻኳ፣ ሴፋ፣ ጋጣታ፣ ዛዳሉዋ፣ ጎጵያ፣ ቱቂያ፣ ድዝግያ፣ ኮጫ፣ እንዳ … የመሳሰሉትን ከውጪ ደግሞ በቤቱ ዙሪያና በአካባቢው የሚገኙ ቆሻሻዎችን በማጽዳት በዓሉን ይቀበሉታል፡፡ እነዚህ ከአባወራ ተግባራት በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ የእማወራዎች ተግባር እማዎራዎች ለጊፋታ በዓል ከሚያደርጉት ዝግጅቶች የመጀመሪያው ”ኦይሳ ቆራጱዋ” ወይም የቅቤ ዕቁብ ሲሆን ይህም ዋንኛው የእማወራ ተግባር ነው፡፡ በዚህም መሠረት ዓመቱን ሙሉ ለጊፋታ የቆጠቡትን ቅቤ በቦቦዳ አጥቢያ ሰብሳቢያዋ ቤት ተሰብስበው የቅቤ ቡና ከጠጡ በኋላ የየድርሻቸውን ተከፋፍለው ይወስዳሉ፡፡ ጊፋታ ካለፈ በኋላም ለቀጣይ ዓመት በየሳምንቱ ቁጠባውን ይቀጥላሉ፡፡ እናቶች ከሰኔ ወር መጨረሻ አካባቢ ለተለያዩ ባህላዊ ምግቦች ማለትም ለቆጮ፤ ለሙቹዋ፤ ለባጪራ፤ የሚሆኑ የደረሱ እንሰቶችን በመፋቅ ዝግጅት ያደርጋሉ፡፡ እንሰት መፋቅ የእናቶች ተግባር ቢሆንም የሚፋቀውን እንሰት መርጦ ማዘጋጀት ግን የአባወራው ተግባር ነው፡፡ በአባወራው ተለይቶ የተሰጠውን እንሰት ጓደኞቿንና ሴት ልጆቿን በማስተባበር መፋቅና ማዘጋጀት የእማወራ ተግባር ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የወላይታ ዳታ በርበሬ ያዘጋጃሉ፤ በዓሉ ሲቃረብ የተለያዩ መጠጦችን ማለትም ቦርዴ፡ ጠላ እና ወተት በታላቅ እንስራ ይዘጋጃል፤ ለልጆች “ጋዚያ” ጨዋታ የሚሆን ሎሚ ገዝተው በቀዝቃዛ ቦታ ያስቀምጣሉ፤ የተለያዩ መዋቢያ ጌጣጌጦችን ይገዛሉ፤ ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ የእህል ዓይነቶችን ገዝተው ያጠራቅማሉ፡፡ በጊፋታ በዓል ዝግጅት የወጣት ወንድ ልጆችና ልጃገረዶች ዋና ተግባር ወንዱ የጉሊያ እንጨት ከመቁረጥ፣ ከማቆምና ከማቃጠል እንዲሁም የማገዶ እንጨት ከመፍለጥ፣ የከብቶችን ሳር አጭዶ ከመከመር ውጪ በአጠቃላይ አባቱ በሚያደርገው እንቅስቃሴ አባቱን የሚረዳ ሲሆን ልጃገረዶችም በመጨረሻው ቀን እንሶስላ ከመሞቅ ውጪ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ እናታቸውን ያግዛሉ፡፡ ዕዳ መክፈል ከጊፋታ በዓል ቅድመ ዝግጅቶች አንዱ ያደረ ዕዳ መክፈል ነው፡፡ በወላይታ ብሔር ሰዎች ከዕዳ ጋር አዲሱን ዓመት አይቀበሉም፡፡ ምክንያቱም የግለሰብም ሆነ የመንግሥት ዕዳ ተሸክሞ አዲሱን ዓመት የሚቀበሉ ከሆነ ዓመቱን በሙሉ ቢያመርትም በረከት የለውም ተብሎ ይታመናል፡፡ ስለሆነም አንድ ገንዘብ ወይም እህል ያስፈለገው ሰው ከሌላ ሰው ሲበደር አበዳሪው ይህ ዕዳ እጅግ ቢዘገይ እስከ ጊፋታ በዓል ድረስ እንደሚመለስ በጣም እርግጠኛ ሆኖ ነው ብድሩን የሚሰጠው፡፡ በመሆኑ በብሄሩ ከጊፋታ በፊት ዕዳን አሟጦ መክፈል የቆየ ነባር ባህል ነው፡፡ በጊፋታ ሳይከፈሉ የዘገዩ ዕዳዎች ሁሉ አዲሱን ዓመት ከመቀበል አስቀድሞ ተሟጠው ይከፈላሉ፡፡ የጊፋታ በዓል ሲቃረብ የሚውሉ ገበያዎች ከእርድ ቀን ቀደም ብሎ የጊፋታ በዓል መቃረቡን የሚያበስሩ በብሔሩ አባላት የሚታወቁ ገበያዎች አሉ፡፡ እነሱም “ሃሬ ሀይቆ”፤ ”ቦቦዶ” እና “ጎሻ” በመባል የሚታወቁ ሲሆን ሌላው ደግሞ “ ቃኤ ጊያ “ ይባላል፡፡ 1. ሃሬ ሀይቆ ””፡- ቀጥተኛ ትርጉሙ የአህያ መሞቻ እንደ ማለት ሲሆን ይህም በወቅቱ ለአህዮች ያለባቸውን ድካም ለማሳየት ነው፡፡ በዓሉ እየተቃረበ በመጣ ቁጥር ሁሉም ሰው ለበዓሉ ዝግጅት እህልና ሌሎችን ቁሳቁሶች በአህዮች እየጫነ ወደ ገበያ ያወጣል፡፡ ይህንን ጊዜ ከሌላዉ የሚለየዉ አንድ አህያ በቀን ከሦስት ጊዜ በላይ እየጫነ ወደ ገበያ ሊመላለስ ይችላል፡፡ በመሆኑም ይህ ወቅት በሕብረተሰቡ የጊፋታ በዓል ዝግጅት ሸመታና ሽያጭ የሚጀምሩበት ነው፡፡ በመሆኑም ከሌሎች ገበያዎች በጣም የተረጋጋ እንቅስቃሴ የሚታይበት ገበያ ነው፡፡ 2. ቦቦዳ“”፡- ሁለተኛው በሃሬ ሀይቆ ሳምንት የሚውለው ገበያ ሲሆን ይህ ገበያ ከወትሮ ለየት ባለ መልኩ በአዳዲስ ነገሮች የተሞላ ገበያ ነው፡፡ በዚህ ገበያ ገበያተኛው በተለመደው ጊዜ ቀድሞ ወደ ገበያ የሚመጣበትና በአብዛኛው ሴቶች የሚበዙበት ነው፡፡ ሴቶች ለበዓሉ የሚያስፈልጋቸውን የቤት ውስጥ ቁሳቁሶች የሚሸምቱበት ሆኖ በዚህ ገበያ የሸክላ ዕቃዎች ሽያጭና ግዥ በእጅጉ ይደራል፡፡ ከዚህም ሌላ በዓሉ እየተቃረበ ከመምጣት ጋር ተያይዞ ሰዎች ሆዳቸውን ባርባር(ፍርሃት ፍርሃት) የሚላቸው ጊዜ እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ የፍርሃቱ ምንጭም ከበዓሉ ትልቅነትና ስፋት አንጻር ምን ይጎልብኝ ይሁን በማለት ቤተሰቡ በሙሉ በፍርሃትና በጭንቀት የሚያሳልፍበት ወቅት ነው፡፡ 3. ጎሻ “”፡- ሶስተኛው ሳምንት ገበያ ጎሻ የሚባል ሲሆን ጥሬ ትርጉሙ እብደት እንደ ማለት ነው፡፡ ሰዎች ከወትሮ በተለዬ ሁኔታ ከንጋቱ 11፡30 ሰዓት ጀምሮ ወደ ገበያ ይሰበሰባሉ፡፡ በገበያ ውስጥ እርስ በርስ የሚገፋፉበት፣የሚገጫጩበት፣እንደ እብድ የሚይዙትን የሚጨባጡትን የሚያጡበት ነገር ግን የማይቀያየሙበት የገበያ ውሎ ነው፡፡ ሴቶች የልጃገረዶችን አልባሳት ማለትም “ማሽኩዋ፣ ግጠቱዋ፣ ጥብቁዋ፣ ሻማጭያ፣ ጎማራ ሀዲያ፣ ዳንጩዋ፣ ሚግዱዋ፣ ሳጋዩዋ፣ ጎዝዳ፣ ዬሌሉዋ፣ ካሎስያ፣ ወሶሉዋ፣ ሎሚያ … ወዘተ” የሚገዙበት ሲሆን ወንዶች ደግሞ ወንድ ልጆቻቸውን አስከትለው ሄደው የወንዶች አልባሳትን ማለትም ቆሊያ፣ ሀዲያ፣ ማሄላንዱዋ፣ ሞጋ፣ ህርቦራ፣ ካላቻ፣ ሁካ፣ ጎፋሪያ ወዘተ የሚገዙበትና በአጠቃላይ ገበያተኛው የሚዋከብበት ገበያ ነው፡፡ ከጊፋታ የእርድ ቀን በኋላ ለሚቀጥሉት 15 ቀናት በየትኛውም አካባቢ ገበያ ስለማይኖር ለበዓሉና ለእነዚህ ጊዜያት የሚበቃ ቁሳቁስና እህል ተሟጦ የሚሸመትበት ነው፡፡ ስለሆነም ሁሉም ሰው በዚህ ሳምንት መረጋጋት የማይታይበት በጥድፊያና በችኮላ የተሞላበት ሳምንት በመሆኑ የዕብድ ገበያ ወይም የዕብደት ሳምንት ይባላል፡፡ ቃኤ ጊያ፡- ሌላው የመጨረሻው ማሳረጊያ ቃኤ ጊያ የሚባል ሲሆን ይህም በእርድ እሁድ ዕለት ማለትም ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ከሌሊቱ 10፡00 እስከ ጧቱ 2፡00 ሰዓት የሚቆም ሲሆን በዚህም ለበዓሉ የሚያስፈልግ ሆኖ ድንገት የተረሳ ነገር ካለ የሚሸመትበት ነው፡፡ ለእርድ እሁድ 15 ቀናት ሲቀሩት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ከበዓሉ ወቅትና ከበዓሉ በኋላ በሚኖሩት የመዝናኛ ሳምንታት ምንም ዓይነት ሥራ ስለማይሠራ ለከብቶች የሚበቃ ሳር በወንድ ልጆች ይታጨዳል፡፡ በአሞሌ ጨው ድርቆሽ ይዘጋጃል፡፡ ከዚህም ሌላ እንጨት በአባቶችና በታላላቅ ወንድ ልጆች ይፈለጣል፤ የቆጮ ቆረጣ በእናቶችና በሴት ልጆቻችው ይደረጋል፤ በድሮ ጊዜ ማሽላና በቆሎ በባህላዊ ወፍጮ ተፈጭቶ ዱቄቱ ይዘጋጃል፤ ዳታ በርበሬ የመለንቀጥ ሥራ በሴቶች ይሠራል፡፡ የጎሻ ሳምንት እየተገባደደ ሲመጣ የሚውለው ሀሙስ “ኮሰታ ሃሙሳ”(ሻጋ ጋላሳ) ይባላል፡፡ ትርጉሙ የእንኩሮ ሃሙስ ማለት ሲሆን ዓርብ ሱልኣ አርባ(ብዛ ጋላሳ) ይባላል፡፡ ይህም በየቤቱ ለቦርዴ የሚሆን እህል የሚዘጋጅበት ሲሆን ለሆድ ማሟሻ ጎዳሬ “” እና ከቦዬ የሚዘጋጅ “” የሚበላበት ዕለት ነው፡፡ ቅዳሜ የባጪራ ቅዳሜ “” የሚባል ሲሆን በዚሁ ዕለት ለእሁድ(የእርድ) ዕለት ሆድ ማለስለሻ ምግቦች ይበላሉ፡፡ በዚህ ዕለት በዋናነት የሚዘጋጁ ምግቦች ባጪራ፣ ሙቹዋ፣ ጉርዱዋ በመባል የሚታወቁ ናቸው፡፡ ሌላው ትልቁ ሥርዓት ደግሞ የእጥበት ሥርዓት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ሌሊት ሁሉም ሰው ልብሳቸውን ያጥባሉ ገላቸውንም ይታጠባሉ፡፡ ይህም ከአሮጌው ዓመት እድፍና ቆሻሻ ጋር ወደ አዲሱ ዓመት መሻገር አያስፈልግም ተብሎ ስለሚታመን ነው፡፡ እሁድ የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ ቀን ሲሆን ከሁለት ወር በፊት በቡድኑ”” አባላት የተገዛው የጊፋታ በሬ በተረኛ የአሙዋ(የቡድኑ) አባል ቤት እሼት በቆሎ፤ስኳር ድንች እንዲሁም ለምለም ሳር አባለቱ በየቀኑ እያዋጡ በደንብ የተቀለበዉ በሬ የሚታረድበት ዕለት ሲሆን የዝግጅት ምዕራፍ ተጠናቆ የመዝናኛ ሳምንት የሚጀመርበት ነው፡፡ የበዓሉ አከባበር የዕርድ ዕለት ጧት ወፍ እንደተንጫጫ በቤተመንግሥት 12 ጊዜ ነጋሪት ይጎሰማል፡፡ በዚህን ጊዜ ከሁሉም የወላይታ አካባቢዎች የአላና ኃላፊዎች ይሰበሰባሉ፡፡ የነጋሪቱን ድምጽ እንደሰሙ የበሬ አራጆች ሥራቸውን ይጀምራሉ፡፡ ከተለያየ ቦታ የመጡ የአላና ኃላፊዎች ወደ ግብር አዳራሽ ይገባሉ፡፡ ቀጥሎም ንጉሱ በክብር ወደ አዳራሹ ከገቡ በኋላ ለሰማይ አምላክ ምስጋና አቅርበው ለበዓሉ የተዘጋጀው ቦርዴ ንጉሱ ከቀመሱ በኋላ እርስ በርስ የፍቅር መግለጫ በሆነው የ”ዳጌታ“ ሥርዓት ይጠጣሉ፡፡ ለበዓሉ የታረደው ሥጋ በዳታ በርበሬ፣ በቂጣና በጎዴታ ቆጮ ይቀርባል፡፡ ሁሉም በልተውና ጠጥተው ወደ የአካባቢያቸው ይመለሳሉ፡፡ ይህም በብሔሩ የጊፋታ “ቃይዴታ” ሥርዓት የሚባል ሲሆን የተጣላ የሚታረቅበት ፍቅራቸውን ከአንድ ማዕድ በመቁረስ የሚያድሱበትና የአዲስ ዓመት ማብሰሪያ ነው፡፡ በዕለቱ የበሬ ሥጋ በጋራ የሚያርዱ የ”አሙዋ” አባላት በየቤታቸው ጠዋት ሙቹዋ ወይም ባጭራ በቅቤ ቡና ይቀምሱና ብላዋና ቅርጫት አስይዘው ወንድ ልጆቻቸውን ወንድ ልጅ ከሌላቸው ሴት ልጆቻቸውን በሬ ወደሚታረድበት ደጃፍ ይሄዳሉ፡፡ የበሬውን ቆዳ ከገፈፉ በኋላ መጀመሪያ ፊኛው ወጥቶ ለልጆች ይሰጣል፡፡ ልጆች ሥጋው ታርዶ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ፊኛ በእግራቸው እየመቱ ይጫወታሉ፡፡ በሬ በሚታረድበት ቤት ደጃፍ የተሰበሰቡ ሰዎች “ባጭራ” ወይም “ሙቹዋ” ከቅቤ ቡና ጋር ይበላሉ፤ባህላዊ መጠጥም ይቀርባል፤ እነዚህ ሰዎች በሬውን በጋራ ያርዳሉ፤ በሬው እየታረደ እያለ ከሁሉም የሥጋው ብልት የተወሰነ ይቆረጥና የ”አሙዋ”አባላት የፍቅር መግለጫ ነው ተብሎ ስለሚታመን በጋራ ይቋደሳሉ፡፡ በመቀጠልም ዕጣ ጥለው ሥጋውን ከተከፋፈሉ በኋላ ለሚቀጥለው ዓመት ጊፋታ በዓል በሬ መግዣ ተቀማጭ በታረደው በሬ ቆዳ ላይ ይጀመራል፡፡ ይህ የቁጠባ ሥርዓት ከ”ጎሉዋ ኢጌታ” በኋላ በየሳምንቱ እስከ ዓመቱ መጨረሻ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የአመጋገብ ሥርዓት የግፋታ ዕለት ከንጋት ጀምሮ ቤት ውስጥ የተለያዩ ዝግጅቶች ይደረጋሉ፡፡ እናቶች ከተዘጋጀው ዳታ ለዕለቱ የሚበቃውን ከፍለው ቅቤ በመጨመር በእሳት ያንተከትካሉ፣ ቂጣ፣ ቆጮ ያዘጋጃሉ፡፡ ከዚህም ሌላ “ኤርጊያ” የሚባላውን ያልተበሳሳ ኮባ ቅጠል ተቆርጦ ሳሎን ላይ በመሬት እንዲዘረጋ ይደረጋል፡፡ አባት ካመጣው ሥጋ መካካል ጥሬ የሚበላውን በማዘጋጀት በቢላዋ እየቆረጠ በኮባው ቅጠል ላይ ዙሪያውን ያስቀምጣል፡፡ ቆጮና ቂጣም በተመሳሳይ ሁኔታ ይደረጋል፤ በመሃል በመሃሉ ዳታ በርበሬ በወጪት ተደርጎ ይቀመጣል፡፡ ማዕዱ ከቀረበ በኋላ ከዓመት ዓመት በሰላም ያሸጋገረውን አምላክ እንደዬ አምልኮ ስርዓታቸው ያመሠግናሉ፡፡ አባት ከሁሉም በፊት ከተዘጋጀው ማዕድ እናትን ያጎርሳል፡፡ በመቀጠል በማዕዱ ዙሪያ የተቀመጡትን ልጆች ሁሉ ያጎርሳቸዋል፡፡ ቀጥሎም የቤተሰቡ አባላት ለየራሳቸው መመገብ ይጀምራሉ፡፡ የጉሊያ አቀጣጠል ሥርዓት ፡- ጉሊያ የወላይታ ብሔር የጊፋታ በዓልን በእሳት ብርሃን የሚያከብረው ሥርዓት ሲሆን የሰኔ “ኩሻ” ወር ማብቂያ ሦስት ቀናት ሲቀሩት የሠፈር ወጣቶች ብዙ አገልግሎት የማይሰጡ እንጨቶችን ከጫካ ውስጥ ቆርጠው እየጎተቱ በአንድ ቦታ ይከምራሉ፡፡ የተከመረው እንጨት ለጊፋታ በዓል ሁለት ሳምንት ሲቀረው እንዲቆም ይደረጋል፡፡ የተከመረው እንጨት የጊፋታ ወር መጀመሪያ ጨረቃ በታየች አራት ቀናት መካከል በሚውለው እሁድ (ሹሃ ወጋ) እርድ ተከናውኖ ሥጋ ከተበላ በኋላ ማታ የሚከበር ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ማታ አንድ ሰዓት አካባቢ የሠፈር ወጣት ወንዶችና አባቶች ከየቤታቸው ቺቦ(ጢፋ) በመያዝ በጉሊያው ዙሪያ ይሰበሰባሉ:: በአካባቢው ታዋቂና ታላቅ የሆነ ሰው ጉሊያውን በእሳት እንዲለኩስ ይጋበዛል፡፡ በዚህን ጊዜ ይህሰው(ሳሮ ላይታ ኦታ፣ ሲቆ ላይታ ኦታ፣ ካሎ ላይታ ኦታ) እያለ በእሳት የተቀጣጠለ ችቦ ይዞ ይዞርና ኡደቱን ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ ዞሮ ከገጠመ በኋላ ጉሊያውን ይለኩሳል፡፡ ከዚያም ከየቤታቸው ያመጡትን ችቦ ይጨምራሉ፣ የጉሊያው ምሶሶ እስኪወድቅ ድረስ ወጣቶች ዞሪያውን ከቦ “ሃያያ ሌኬ” የሚባለውን ባህላዊ ዘፈን ይዘፍናሉ፤ ይጨፍራሉ፡፡ ሥጋ ከተበላ በኋላ ልጃገረዶች በአካባቢው ጉሊያ ወደሚቀጣጠልበት ቦታ በመሄድ ክብ ይሠሩና የጊፋታን ጨዋታ እየተጫወቱ ያመሻሉ፤ በመጨረሻ በቀጥታ በአካባቢው አዲስ ሙሽራ ካለች ወደሷ ቤት በመሄድ እየዘፈኑና እየጨፈሩ ይቆያሉ፤ እኩለ ሌሊት ሲደርስ ቀን በዛ ቤት ተፍቆ አዘጋጅቶ ያስቀመጡትን እንሶስላ ይሞቃሉ፡፡ ከእርድ በኋላ ከፍ ብሎ እንደተጠቀሰው በእርድ ዕለት ማታ ጉሊያ የማቃጠል ሥርዓት የሚፈጸም ሲሆን የእርድ ዕሁድ ማግስት ሰኞ ታማ ሰይኖ ይባላል፡፡ ጥሬ ትርጉሙ የእሳት ሰኞ ማለት ነው፡፡ ይህም እሁድ ዕለት በሁሉም ሰው ቤት እስከ ሌሊት ድረስ እሳት ስለሚነድ በነጋታው ሰኞ ማንም ሰው ወደ ጎረቤቱ እሳት ለመጫር አይሄድም፡፡ ምክንያቱም የእሳቱ ፍም በነጋታውም ቢሆን በሁሉም ቤት አይጠፋም፡፡ በዚህ ቀን ከሚከናወኑ ተግባራት አንዱ የተረፈው ሥጋ ተዘልዝሎ እሳት በምድጃው ላይ በደንብ እንዲነድ ተደርጉ በምድጃው ግራና ቀኝ ባላ እንጨት ተተክሎ ተዘልዝሎ ይጠበስና ማባያ ተዘጋጅቶ ሁሉም ተሰብስበው ይበላሉ ይጠጣሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በዚህ ቀን ቶሎ የሚበላሹ የሥጋ ዓይነቶችን በእሳት በማገንፈል ጨው አዘጋጅቶ በማከም ለረዥም ጊዜ እንዲቆይ ያደርጋሉ፡፡ ከግፋታ ቀጥሎ የሚመጣው ሁለተኛው ቀን ማክሰኞ “ጪሻ ማስቃይኖ” ይባላል፡፡ ይህም የመልካም ምኞት አበባ የሚለዋወጡበት ቀን ነው፡፡ በዚሁ ዕለት የአዲስ ዓመት ማብሰሪያ “ኮርማ ጪሻ” ተብሎ የሚጠራው ነጭ አበባ ይህ ካልተገኘ ደግሞ የአደይ አበባ የተባለው የአበባ ዓይነት ተይዞ እንኳን አደረሳችሁ! ጊፋታ ዮዮ! እየተባለ አማች፣ አበልጅ ቤት እንዲሁም ደግሞ እንደየቅርበቱ ዘመድ አዝማድ ቤት እየተኬደ መልካም ምኞታቸውን የሚገልጹበት ዕለት ነዉ፡፡ አበባውን ይዘው ከሄዱ በኋላ ለቤቱ አባወራ የሚሰጥ ሲሆን እሱም በቀኝ እጁ ይቀበልና ከምሶሶ ጋር ያስራል፡፡ እነዚህ ሁለት ዓይነት አበቦች በጊፋታ ወቅት ብቻ የሚፈኩ አበቦች ስለሆኑ አባወራው አበባዉን ከተቀበለ በኋላ ጊፋታ እናንተን አይቁጠር እናንተ ጊፋታን ቁጠሩ “” ከዓመተ ዓመት በሰላም ያድርሳችሁ በማለት ይመርቃሉ፡፡ ከዚያም የሚበላና የሚጠጣ ነገር ተጋብዘው ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ፡፡ በነጋታው ጋዜ ኦሩዋ ”” ሲሆን ይህም ሰዎች አጠቃላይ ሀሳባቸውን ወደ መዝናኛ የሚያደርጉበት ሆኖ ታላቁ የጊፋታ ጨዋታ ጋዚያ” ”መድመቅ የሚጀምርበት ዕለት ነዉ፡፡ በዚህ በተከታታይ ለሁለት ሳምንታት በሚቆየዉ ጨዋታ የመንደሩ ወጣት ወንዶችና ወጣት ሴቶች በአካባቢው ታዋቂ ሽማግሌ ደጃፍ ተሰብስበው ወንዶች ሃያያ ሌኬ እያሉ ትከሻ ለትከሻ ተቃቅፈው ሎሚ ከልጃገረዶች በመለመን ለትዳር የሚፈልጓትን የሚመርጡበትና የሚያባብሉበት ሴቶችም ደግሞ እንደ አስፈላጊነቱ ምላሽ እየሰጡ የሚጫወቱት የጨዋታ ዓይነት ነው፡፡ በጋዚያ ወጣቶች ይዘፍናሉ፤ ትግል ይገጥማሉ፤ ሩጫ ይወዳደራሉ፤ የፈረስ ጉግስ ይደረጋል፤ ሎሚ ከልጃገረዶች ላይ ይለምናሉ፡፡ ልጃገረዶች አንድ ላይ በመሆን በየቡድኑ ተከፋፍለው ተቀምጠው “ሀያ ወላሎሜ” እያሉ ለወንዶች ሎሚ በመወርወር ይመርጣሉ፡፡ አንዳቸው ለሌላው ልዩ ሚስጥረኛ ይሆናሉ፤ ከዚያን ዕለት ጀምረው በስማቸው ሳይሆን የሚጠራሩት “ሎሜ ሎሜ” በማለት እርስ በርስ ይጠራራሉ፡፡ ሌላው ደግሞ ልጃገረዶች እርስ በርስ ለሚዜነት ከሚመርጧት ጋር አንድ ሎሚ በጥርሳቸው በጋራ በመካፈል እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ድረስ እርስ በርስ ሚስጥር በመጠበቅ የልብ ጓደኛሞች ይሆናሉ፡፡ በጋዚያ ቦታ ወላጆች የልጆቻቸውን ጨዋታ ለማየት አልፎ አልፎ ይመጣሉ፡፡ እርስ በርስ እንዳይጣሉና ግጭት እንዳይፈጠር እንዲሁም ደግሞ ጠለፋ እንዳይፈጸም ይከታተላሉ፡፡ በዚያ ቦታ ከጓደኞቻቸው ጋር በመገናኘት ”!“ በመባባል እርስ በራሳቸው ይጫወታሉ፤ በመጨረሻም አንድ ላይ ተቃቅፈው ለዘለዓለም እንኖራለን ”” በማለት አንዱ ለሌላው መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡ ከጋዜ ኦሩዋ ጀምሮ ተቆጥሮ የሚመጣው ሶስተኛ ረቡዕ ጎሏ ኦሩዋ ”” ይባላል፡፡ ይህም ከአንድ ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ የቆየው የበዓል ዝግጅትና አጠቃላይ የጊፋታ በዓል ሥነ-ሥርዓት አብቅቶ የሚሸኝበት ቀን ሲሆን ከበዓሉ ጋር ተያይዞ በነበረው የመዝናኛ ወቅት ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ስንፍና እንዳይገባ በማለት ሁሉም ችቦ እያቀጣጠሉ ለሚመጣው በዓል አምላክ በሰላም እንዲያደርሳቸው በመመኛት ይሸኛሉ፡፡ ይህም የመዝናኛ የዕረፍት ወቅት አብቅቶ ወደ ሥራ የሚገባበት ወቅት በመሆኑ “” ይባላል፡፡ ይህም ከዕሮብ በኋላ ዕረፍትና መዝናናት የለም የሥራ ወቅት ተጀምሯል፤ ወደ ሥራ አንግባ እንደማለት ነው፡፡
8413
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%96%E1%88%AD%E1%89%B1%E1%8C%8B%E1%88%8D
ፖርቱጋል
ፖርቱጋል ወይም ፖርቹጋል (ፖርቱጊዝኛ፦ /ፑርቱጋል/) በኤውሮፓ ውስጥ የሚገኝ ሀገር ነው። የፖርቹጋል መንግሥት በምዕራብና በደቡብ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ፤ በምሥራቅና በሰሜን ከኤስፓኝ መንግሥት ጋር ይዋሰናል። የፖርቱጋል ስም ከአንድ ሮማይስጥ ወደብ ስም /ፖርቱስ ካሌ/ («የካሌ ወደብ»፣ የአሁንም ፖርቱ) መጥቷል። የ«ካሌ» ትርጉም እዚህ ቢካራከርም ዋናው አስተሳሰብ ከጋሊስያ (የእስፓንያ ክፍላገር) እና ከጥንቱ ጋላይኪ ወገን (ኬልቶች) ጋር እንደ ተዘመደ የሚለው ነው። በየጥቂቱ የሮማይስጥ አጠራር /ፖርቱስ ካሌ/ ወደ /ፖርቱካሌ/ (400 ዓም ግ.)፣ እና /ፖርቱጋሌ/ (600 ዓም ግ.) ተለወጠ፣ ከ800 ዓም ግ. በኋላ ለመላው አውራጃ ይጠቀም ጀመር። «ፖርቱጋል» () የሚለው አጻጻፍ ከ1000 ዓም ግድም ጀምሮ ሲገኝ፣ በአማርኛ ደግሞ የአገሩ ስም እንደ እንግሊዝኛው አጠራር እንደ ፖርቹጋል ሊጻፍ ይችላል። የብርቱካን ፍራፍሬ፣ ዛፍ፣ ቀለም ስም ደግሞ ከፖርቱጋል ስም ደርሶልናል። የፖርቹጋል የጥንት ስም ሉዚታኒ ነው። በመጀመሪያም በአገሪቱ የነበሩት ሕዝቦች ሴልቶ ኢቤሪክ የሚባሉ የህንዶ-ኤውሮፓዊ ወገን ሆነው በኋላ ወደ ላቲንነት በልማድና በኑሮ በሃይማኖትም የተለወጡ ናቸው። የፖርቱጋል ሕዝብ በጀርመንና በኖርማንዲ በሮማውያንና በዐረቦች ሞሪ (ማውሪታኒ) ከሚባሉ በአፍሪካ ሰሜን ሕዝብና በዕብራውያንም የተቀያየጠ ነው። ነገር ግን እነዚህ ሁሉ ባንድነት ሰፊ ዘመን በሮማ መንግሥት ስለ ተገዙ በዘርም በልማድም አብዛኛውም ወደ ላቲንነት ተለውጠዋል። የሮማ መንግሥት ከወደቀ በኋላ በአምስተኛውና በስምንተኛው መቶ ዓመተ ምሕረት መካከል በነበረው ጊዜ ውስጥ እየተከታተለ ቢዚጎትና ስቤብ የሚባሉ የጀርመኖች ቀጥሎም የዐረቦች ወረራ ደርሶባቸዋል። በአስረኛው መቶ ዓ.ም. ግን አስቱሪዩ የሚባሉት የክርስቲያን ወገኖች እስላሞቹን አጥፍተው ሊስቦን ገብተው ገዥ ሆነው መንግሥታቸውን አቋቋሙ። ከዚያ ከ፲፪ እስከ ፲፬ መቶ ዓ.ም ድረስ ቤተ መንግሥቱን የቡርጎኝ ሥርወ መንግሥት ሲገዛው ቆይቶ በኋላ ሔቢዝ ለተባለው ቤተ መንግሥት አሳለፈው። በነዚህ መሪነት ጊዜ ይኸውም ማለት በ፲፬ኛውና በ፲፭ኛው መቶ ዓመተ ምሕረት ላይ የፖርቱጋል መንግሥት ከሌላው ሁሉ ይልቁንም በባሕርና በመርከብ ኃይል ሆነ። በዚህ በ፲፭ኛው መቶ ዓ.ም. ላይ የቱርክ፣ የመስኮብ፤ የጀርመን፤ የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይና የኤስፓኝ መንግሥታት እንደ ኃያላን መንግሥታት መቆጠራቸው አልቀረም። ነገር ግን ከነዚህ ሁሉ የፖርቱጋል መንግሥት በሌላው እንኳን ባይሆን በመርከብና አገር በመያዝ ከቀሩት ይበልጥ ነበር። የቀሩት የኤውሮፓ መንግሥታት እዚያው ወሰናቸው ላይ ገዥነታቸውን ለማጽደቅ እርስ በርሳቸው ሲጨቃጨቁ የፖርቱጋል መንግሥት ግን ደኅና ደኅና መርከቦችን አዘጋጅቶ እየላከ ከመንግሥቱና ከኤውሮፓ ርቆ የሚገኘውን የአሜሪካን፤ የእስያን፤ የአፍሪካን አገሮች ያስመረምር ነበር። መርማሪዎቹም እነቫስኮ ደጋማ፤ እነፔሬዝ፤ እነአንድራድ፤ እነካብራል በመርከብ እየሄዱ ለመከላከል ጉልበት የሌለውንና በጠባዩ ሀብት ያለበትን አገር መርምረው ሲመለሱ መንግሥቱ ወታደር በመርከብ እየላከ ብዙ አገር ያዘ። በሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፭፻ እ.ኤ.አ. ፔድሮ አልቫሬዝ ካብራል የተባለው የፖርቱጋል መኮንን በትልቅ መርከብ ሄዶ ይን ጊዜ ለቀረው ዓለም ያልታወቀውን የብራዚልን አገር አስገበረና በፖርቱጋል መንግሥት ስም ቅኝ አገር አደረገው። ከዚያም አገር በተገኘው ወርቅ መንግሥቱ ሀብታም ሆነ። እንደዚሁም የመጀመሪያ የንጉሥ እንደራሴ የተባለው ፍራንቼስኮ ዳልሜዳ ወደ ህንድ አገር ሄዶ አገሩን ያዘ። ከተማውንም በጎአ አድርጎ ህንድንም የፖርቱጋል የቄሣር ግዛት አደረገና አገር ገዥውም የንጉሥ እንደራሴ ይባል ጀመር። ከዚያም በትልቁ ውቅያኖስ ውስጥ የሚገኙትን ደሴቶች ኑቤል ጉኔንና ዛሬ ፊሊፒን የሚባለውን አገር በየጊዜው በጦር ኃይል አስገበራቸው። በዚሁ አኳኋን ወደ ኢትዮጵያም እነኮቪልሐኦ ቀደም ብለው በዓፄ እስክንድር ዘመን መጥተው እንደመረመሩትና የኢትዮጵያ መንግሥት በዚያ ጊዜ በነሱ አጠራር የቄሱ የዮሐንስ መንግሥት አለ ብለው አውርተው እንደነበረ ሌላ የፖርቱጋል የጦር መርከብ በአፍሪካ ድንበር በቀይ ባሕር ላይም እየተመላለሰ አስቀድሞ ከያዙት ከቱርኮችና ከግብጾች እየተዋጋ አንድ ጊዜም እየተሸነፈ አንድ ጊዜም እያሸነፈ ብዙ ጊዜ ተመላለሰ። በዚህ ሁሉ ምክንያት የፖርቱጋል መንግሥት ታላቅነት በሌላው ዓለም እንደ ታወቀ እንደዚሁም ፩ኛ ትልቅ መንግሥት መሆኑ ፪ኛ ክርስቲያን መሆኑ ኢትዮጵያ ባሉት የውጭ አገር ሰዎች አፍ እየተነገረ ዝናው በኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት ዘንድ መሰማት ቻለ። ደግሞ ይዩ ዋቢ ምንጭ
39084
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A3%E1%89%A2%E1%88%8C%20%E1%8B%A8%E1%8B%9D%E1%88%86%E1%8A%95%20%E1%88%98%E1%8C%A0%E1%88%88%E1%8B%AB
ባቢሌ የዝሆን መጠለያ
ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ () ከአዲስ አበባ ወደ ጅጅጋ መስመር፣ ፭መቶ ፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ይህ መጠለያ በቆዳ ስፋት ፮ሺ ፱መቶ ፹፪ ካሬ-ሜትር የሚመዘን ሲሆን፣ ከጠቅላላ ስፋቱም ውስጥ ፸፯ ከመቶ ያህሉ በአሁኑ አጠራር ”በሶማሌያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ሲካለል፤ ቀሪው ፳፫ ከመቶ ያህሉ ደግሞ ”በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ይገኛል። የአካባቢው የኦሮሚያ ብሔር ተወላጆች ‹‹ወረ-ሃርባ›› (ባለዝሆኖቹ) በማለት የሚጠሩትና በፌዴራል የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ሥር የሚተዳደረው የባቢሌ ዝሆኖች መጠለያ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት፣ በ፲፱፻፷፪ ነው የተመሠረተው። የምሥረታውም ዋነኛ ዓላማ፥ በምሥራቅ አፍሪካ ብቻ የሚገኙትን “ሎክሶዳንታ አፍሪካና ኦርሊያንሲ” የተባሉትን ንዑስ የዝሆን ዝርያ ለማልማትና ለመጠበቅ ሲሆን ባሁን ጊዜ መጠለያው በተጨማሪም ከ፴ በላይ ጡት አጥቢ የዱር እንስሳት፣ ከ፪መቶ ፶ በላይ የአዕዋፍ ዝርያዎች፣ ፫መቶ ያህል የዕፅዋት ዝርያዎች የሚገኙበት ነው። ከሌሎች አዕዋፍ እና የዱር አራዊት ዝርያዎች ደግሞ ከገጸ ምድር የመጥፋት አደጋ ላይ ያለው ”የሳልቫዶሪ ዘረ-በል” () ወፍ እና ባለጥቁር ጎፈር አንበሳ በዚህ መጠለያ ይገኛሉ። የባቢሌ ዝሆኖች መጠለያ ከተመሠረተበት ዘመን ወዲህ ለመቋቋም ከተገደደባቸው ክስተቶች መካከል የኢትዮጵያና የሶማሊያን ጦርነት ያስከተለው ቀድሞ በዳካታና ፋፈም ሸለቆዎች የነበሩ ዝሆኖች ወደ ኤረር ሸለቆ የሸሹበት ሁኔታ ነበር። ሌላው አደገኛ ክስተት ደግሞ በመጠለያው ውስጥ የሰው ሠፈራ የተከለከለ ቢሆንም ከቁጥጥር ያለመኖር ምክንያት ባለፉት ፵ ዓመታት ቀስ በቀስ በሰው-ሠራሽ ተፅዕኖ መጠለያው ከፍተኛ ግፊት ላይ ወድቋል። በተለይም ከ፲፱፻፺፮ ዓ/ም ወዲህ በመጠለያው ውስጥ እየጨመረ የመጣውን ‹‹ሕገ-ወጥ›› ሠፈራና ሰው-ሠራሽ ተፅዕኖዎች ለመግታት በቂ የጥበቃ ኃይል ባለመሰማራቱና የሠፈሩትንም በሕጋዊ መንገድ የማስለቀቅ የፖለቲካዊ ቆራጥነትም ሆነ ከሙስና የጸዳ አሠራርም ባለመኖሩ የዱር አራዊቱ ስደት እና ዕልቂት እየተባባሰ እንደሆነ የቅርብ ጊዜ ዘገባዎች ያመላክታሉ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ይሄንን አስጊ ሁኔታ በተመለከተ በቅርቡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የባህል፣ቱሪዝምና የብዙሃን መገናኛ ጉዳዮች ቋሚ ኮሜቴ አባላት በስፍራው ተገኝተው ባደርጉት ምርምር ላይ የሰጡትን ገለጻ በመጥቀስ፣ ሕገ-ወጥ ሰፈራ፣ የመጠለያ ድንበር የማከለሉ ሥራ አለመተግበር፤ አርብቶ አደሮች ከብቶቻቸውን በመጠለያው ማኖር ለመጠለያው አደጋ ላይ መውደቅ ተጠቃሽ ምክንያቶች መህናቸውን ዘግቧል። ከሁሉም በላይ ግን ከፍ ያለ ውዝግብ እና ዓለም-አቀፍ ተቃውሞ ያስከተለው በ፲፱፻፺፯/፲፱፻፺፰ «ፍሎራ ኢኮ ፓወር» () ለተባለ የንምሳ ኩባንያ ለናፍጣ-ነዳጅ ማምረቻ የሚሆን የጉሎ ተክል ልማት ተብሎ በተፈቀደለት፤ ወደ አሥራ-ሁለት ሺ ሄክታር መሬት ላይ ያደረሰው የመጠለያውን ደን ምንጠራ ነው። ኩባንያው በፌዴራል መንግሥቱ ቡራኬ ከኦርሚያ ብሔራዊ መንግሥት የተረከበው ይህ ‘የልማት’ መሬት ፹፯ በመቶው በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ክልል ላይ ያረፈ መሆኑን በፌዴራሉ መንግሥት ምርመራ ተረጋግጦ ቢሆንም ምርመራው የተካሄደው ኩባንያው ደኑን ከመነጠረ በኋላ ስለነበር የዝሆኖቹን የሽግግር ወቅት ያዛባበት፣ ከዚህ ቀደም ወደማይንቀሳቀሱበትና ከመጠለያው ክልል ውጪ ወደሆኑ ቦታዎች እንዲገፉ ተፅዕኖ እንዳደረገ ይገመታል። «ፍሎራ ኢኮ ፓወር» የጀመረው የጉሎ ልማት ስኬታማ ሳይሆንና አገሪቱም ከታሰበው ነዳጅ አንዳችም ጠብታ ሳታይ ኩባንያው ዕዳውንም ሳይከፍል ከአገር እንደወጣ በሰፊው ተዘግቧል። ዋቢ ምንጮች ቁም ነገር መፅሔት የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን የኢትዮጵያ እንስሳት መዝናናት
23099
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%A5%E1%88%8B%E1%88%B4
ሥላሴ
ሥላሴ ማለት ሠለሰ ከሚል ቃል የመጣ ሲሆን ሦስትነት ማለት ነው፣ ቃሉም የግእዝ ነው። ይህ ቃል የአምላክን አንድነትና ሦስትነትን ያመለክታል። የሥላሴ እምነት የክርስትና ሃይማኖቶች ተከታይ አንዷ ከሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዋነኛ መሰረተ ትምህርት ነው። ትምህርቱ በዐቢይ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ (ተዋሕዶ፣ ምሥራቅ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክና ፕሮቴስታንት) ዘንድ ተቀባይ ሲሆን ማለትም በእንግሊዘኛ ሞኖቴዪዝም (= በአንድ አምላክ ማመን) ይባላል፣ የሥላሴን አንድነት ያልተረዱ ወይም መረዳት የማይፈልጉ ፖሊቴዪዝም (በብዙ አምላክ ማመን= ) ብለው ይሰይሙታል ፣ ደግሞ ከማያስተምሩት ክፍልፋዮች መካከል አሪያኒስም፣ የይሖዋ ምስክሮች፣ እና ሞርሞኒስም ተገኝተዋል። ከድረ ገፃቸው አንዱን ለማየት እዚህላይ ይጫኑ አጭር መረጃ ትምህርተ ሥላሴ እንደሚለን፣ እግዚአብሔር ፈጣሪ አንድላይ በሦስት ቦታዎች ሊኖር ይችላል። ፩) በመሢሕ ይኖራል (ወልድ)፤ ፪) በልባችን ይኖራል (መንፈስ ቅዱስ)፤ ፫) በማይታይ ሰማያት የትም ቦታ ይኖራል (አብ)። በአትናቴዎስ ሃይማኖታዊ ድንጋጌ መሰረት ሁሉም ዘላለማዊ የሆኑ፣ እያንዳንዳቸው ሁሉን ማድረግ የሚችሉ፣ አንዳቸው ከአንዳቸው የማይበላለጡ፣ ሁሉም አምላክ የሆኑ ሦስት መለኮታዊ አካላት (አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ) አሉ። ይሁን እንጂ ሦስቱም አንድ አምላክ ናቸው እንጂ ሦስት አማልክት አይደሉም። ስለዚህ ቀኖና የተሰጡ ሌሎች መግለጫዎች እንደሚያመለክቱት እነዚህ ሦስት "አካላት" መለኮታዊው ህልውና የሚገለጥባቸው ሦስት መንገዶች ናቸው እንጂ የተለያዩና ግላዊ ሕልውና ያላቸው "አካላት" አይደሉም። በዚህም ምክንያት አንዳንድ የሥላሴ አማኞች ኢየሱስ እግዚአብሔር እንደሆነ ወይም ኢየሱስና መንፈስ ቅዱስ ይሖዋ እንደሆኑ አጥብቀው ያምናሉ። አምላክ አንድ ሲሆን ሶስት ሶስት ሲሆን አንድ ማለት ነው፤ በስም፣ በአካል እና በግብር ሶስት ሲሆን በህላዌ እና በመለኮት አንድ ነው። ክርስቶስ ከመወለዱ በፊት የሥላሴ ሦሥትነትና አንድነት በብሉይ ኪዳን ብዙ ቦታ ተጽፎ ይገኛል። ነገር ግን በዛን ወቅት የነበሩ ነብያትም ሆኑ አስተማሪዎች ነገሩ አልተገለፀላቸውም ነበር። በግልፅ በመጻሕፍ ቅዱስ ውስጥ ከሚነበቡት፦ አዳምን በአምሳላችን እንፍጠር ፣ አዳም እንደኛ አንዱ ሆነ ፣ የሰናዖርን ሰዎች ቋንቋ በመለያየታቸው ፣ በአብርሃም ቤት በመስተናገዳቸው ዳዊት በመዝሙር ብሎ በጻፈው… ክርስቶስ ከመጣ በኋላ ግን የተሸፈነው ሁሉ ተገልጾ በተግባር አንድም ሦሥትም መሆናቸውን ኢየሱስ አሳወቀም አስተማረም በእየሩሳሌም በበዐል ቀን ጠፍቶ ሲገኝ ለእናቱ ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ና ለቅዱስ ዮሴፍ ሲመልስ በማለቱ፣ በዮርዳኖስ ጥምቀቱ ፡ ባለው፣ በደብረ ታቦር የጌትነቱ ግርማ ማለትም መላ ሰውነቱና ልብሱ በሚያስደንቅ ብርሃን በመሞላቱ ፣ ለፍሊጶስ እኔን ካያቹህ አብን አባቴን እንዳያቹህ ቁጠሩ፣ አባታችን ሆይ ጸሎት በማስተማሩ… ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ከዐረገ በኋላም፦ በቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ጊዜ በሐዋ.ሥ.-ም፡፯ ቁ፡፶፭-፶፮ ላይ እንደተጻፈው የዮሐንስ ወንጌል ም፡፭ ቁ፲፮-፵፮ እነዚህ ከብዙዎቹ ጥቂጦቹ ሲሆኑ በይበልጥ ለመረዳት ይህን ይጫኑ: ሰይፈ ሥላሴ ወይም እዚህ ይጫኑ ደግሞ ይዩ፦ የንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት የተሰሎንቄ ዐዋጅ። የሥላሴ እምነት ምንጭ የሥላሴ እምነት ደጋፊዎች በተለይ ማቴ. ፳፰፡፲፱ ያጠቁማሉ። ሆኖም ተቀራኒ ድምጾች እንደሚሉ ይህ ጥቅስ በኋላ ነበር ወደ ወንጌሉ የተጨመረው። ከዚህም ሁሉ በላይ የሥላሴ ትምህርት የሚቀበሉት አብያተ ክርስትያናት ፪ ቆሮንቶስ ፲፫፡፲፬ እና ፩ ቆሮንቶስ ፲፪፡፬-፮ ሲያመለከቱ፣ ይህ እምነት ከመጀመርያ ደቀ መዛሙርት ጀምሮ እንደ ተመሠረተ ለማስረዳት ይጣራሉ። ዳሩ ግን ሌሎች መምህሮች ለነዚህ ነጥቦች ትልቅ ስፍራ አይሠጡም። በእንግሊዝኛ የተጻፈው ዘ ኒው ኢንሳይክሎፔድያ ብሪታኒካ እንዲህ ይላል፦ «ሥላሴ የሚለው ቃልም ሆነ በግልጽ የተብራራ የሥላሴ መሰረተ ትምህርት በአዲስ ኪዳን ውስጥ አይገኝም። ኢየሱስም ሆነ ተከታዮቹ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተጻፈውን፦ 'እስራኤል ሆይ ስማ፣ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው' (ዘዳግም ፮፡፬) የሚለውን ለማስተባበል አላሰቡም። . . . የሥላሴ እምነት ቀስ በቀስ የተስፋፋው በበርካታ መቶ ዓመታት ውስጥ ከብዙ ንትርክ በኋላ ነው። . . . የሥላሴ መሰረተ ትምህርት አሁን ያለውን ቅርጽ የያዘው በአራተኛው መቶ ዘመን መጨረሻ ላይ ነው።» ሚስጥረ ሥላሴ የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት በምንማርበት ጊዜ ከሂሳብ ቀመር ህግ አስተሳሰብ ውጭ ሆነን ነው ። ይህን የምንልበት ሥላሴ አንድም ሦስትም ሦስትም አንድም ናቸው ስንል የሃይማኖት አባቶች በሒሳብ ቀመር ፩ ፫ እንዳልሆነ ፫ ፩ እንዳልሆነ ጠፍቶባቸው አይደለም ስሌቱ መንፈሳዊ ይዘት ስላለው ነው። ሌላው ምክንያት መንፈሳዊዉ ሥጋዊዉን ጥበብ ይመረምረዋል እንጅ መንፈሳዊ ጥበብና ምሥጢር በዓለማዊ ዕውቀት ምርምር ሊደረስበት አይቻልምና ። እግዚአብሔር በጥሩ መንፈስ፣ በቅን ልቦና፣ ፈሪሐ እግዚአብሔር ባለው ፍለጋ ከፈለጉት ለማንኛውም ሰው ፈላስፋም ይሁን ገበሬ ይገለፃል። እሱን ለመቃረን ፍለጋ ከተነሱ ግን ወደ ዋና አውሬ መሄጃውን መንገድ ያስይዛል ምክኒያቱም ሌላ ምንም ምርጫ ስለሌለ እንደተጻፈው "በተመኙት ላይ ጨምሮ ይሰጣል"። ሚሥጥረ ሥላሴ ሚሥጥረ ሥጋዌ ሚሥጥረ ጥምቀት ሚሥጥረ ቁርባን ሚሥጥረ ትንሣኤ ሙታን እነዚህ ፭ አዕማደ ሚሥጥራት ሰለ ሥላሴ ቁልጭ ያለ አመለካከት እንዲኖረን ያደርጋሉ ፣ እንዲየውም ማንኛውም የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ተከታይ ሚሥጥሮቹን ሁሉ ማወቅ ይጠበቅበታል። መጽሐፍ ቅዱስ
13542
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%82%E1%88%A9%E1%89%B5%20%E1%89%A0%E1%89%80%E1%88%88
ሂሩት በቀለ
ሂሩት በቀለ ( ሂሩት በቀለ ከ50ዎቹ መጀመሪያ እስከ 80ዎቹ መጨረሻ ድረስ በጊዜው ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ጥቂት ስመጥር የሴት አርቲስቶች መሐከል አንዷ ተወዳጅ ድምፃዊት የነበረች ስትሆን: በተጨማሪም የግጥምና የዜማ ደራሲ ነበረች:: ሂሩት የተጫወተቻቸው ዘመን ተሻጋሪ ሙዚቃዋቿ እስከ አሁን ድረስ በህዝብ ዘንድ በጣም ተወዳጅና እንደውም ለብዙ አዳዲስ ወጣት ሴት አርቲስቶች መነሳሻና አቅም መፈተሻ የነበሩ መሆናቸው ግልጽ ነው። የህይወት ታሪክ ሂሩት በቀለ እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በእለተ ሰኞ መስከረም 28 ቀን 1935 ዓ.ም. ከእናቷ ከወ/ሮ ተናኜወርቅ መኮንንና ከአባቷ የመቶ አለቃ በቀለ ክንፌ በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ቀበና ተወለደች:: እድሜዋ ለትምህርት ሲደርስም ቀበና ሚሲዩን ት/ቤት በመግባት የአንደኛ ደረጃ ትምህርቷ ተከታትላለች:: የስራ ዝርዝር ሂሩት በትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ለክፍል ጏደኞቿና ለሰፈሯ ልጆች ማንጎራጎር ታዘወትር ነበር:: ይህን ችሎታዋን የተመለከቱት ጏደኞቿም ወደሙዚቃው አለም እንድትገባ በተደጋጋሚ ያበረታቷትና ይገፏፏት ነበር:: በዚህ መሰረት እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በ1951 ዓ.ም. ከቅርብ ጏደኛዋ ጋር በመሆን ወደ ምድር ጦር ሙዚቃ ክፍል በመሄድ በድምፃዊነት ተፈትና ለመቀጠር በቃች:: ብዙም ሳትቆይ ለመጀመሪያ ግዜ በተጫወተችው “የሐር ሸረሪት” በተሰኘው ዜማ በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትንና ተቀባይነትን አገኘች:: ይሄኔ ነበር የፖሊስ ሰራዊት ኦርኬስትራ ክፍል አይኑን የጣለባት። ጥሎባትም አልቀረ በ 1952 ዓ.ም. ላይ ከምድር ጦር ሙዚቃ ክፍል እውቅና ውጪ የፖሊስ ሰራዊት ኦርኬስትራ ሂሩትን በመጥለፍ በጊዜው ኮልፌ ፈጥኖ ደራሽ ወደሚባለው የፖሊስ ማሰልጠኛ ካምፕ በመውሰድ በልዩ ኮማንዶዎች የ24 ሰዓት ጥበቃ እየተደረገላት ለበርካታ ወራቶች ተደብቃ ቆየች:: ከረጅም ወራቶች ያላሰለሰ ጥረት በኃላ የምድር ጦር ሙዚቃ ክፍል ፍለጋውን ለማቋረጥ በመገደዱ: የፖሊስ ሰራዊት ኦርኬስትራ ክፍል ሂሩትን በይፋ በቋሚነት የሠራዊቱ የሙዚቃ ክፍል አባል አድርጎ ቀጠራት:: ሂሩት ከተጫወተቻቸው አያሌ ሙዚቃዎቿ መሀከል አንደ ህዝብ መዝሙር በአገር አቀፍ ደረጃ የሚታወቀውና ከትንሽ እስከ ትልቅ በሀገር ፍቅር ስሜት እስከአሁን የሚያዜመው “ኢትዮጵያ” አንዱ ነው:: ሂሩት በፖሊስ ሰራዊት የሙዚቃና የትያትር ክፍል ውስጥ በቅንነት ለ35 ዓመት አገልግላለች:: በነዚህም 35 ዓመታት ውስጥ ከ­­­200 በላይ ሙዚቃዎችን የተጫወተችና ለህዝብ ጆሮ ያደረሰች ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በሸክላ የታተሙት ከ38 በላይ ሙዚቃዎች ሲሆኑ: በካሴት ደረጃ ደግሞ 14 ካሴቶች እያንዳዳቸው 10 ዘፈኖችን የሚይዙ ለሙዚቃ አፍቃሪዎቿ አበርክታለች:: ሂሩት በሙዚቃ አለም በቆየችባቸው አያሌ አመታት ውስጥ ከብዙ ስመጥር ድምፃውያን ጋር በመሆን ስራዋን ለህዝብ አቅርባለች: ከነዚህም መሀከል ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል: ማህሙድ አህመድ: አለማየሁ እሸቴ: ቴዎድሮስ ታደሰ: መልካሙ ተበጀ: ታደለ በቀለ: መስፍን ሀይሌ: ካሳሁን ገርማሞና ሌሎችም ይገኙበታል። ሂሩት በቀለ ከ1987 ዓ.ም. በኃላ እራስዋን ከሙዚቃ አለም በማግለል ጌታን እንደግል አዳኟ በመቀበል ሙሉ ጊዜዋንና ህይወቷን ለመንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ከ28 ዓመት በላይ በአገር ውስጥና በውጭ አገር በመዘዋወር ስለጌታችን እየሱስ ክርስቶ ታላቅነት ላልሰሙ በማሰማት አያሌ ወገኖች የእግዚህአብሄርን መንገድ እንዲከተሉና ወደ ህይወት እንዲመጡ ምስክርነት በመስጠት: በጸሎት በመትጋት ጌታን በዝማሬ እያገለገለች ትገኛለች:: ሂሩት በቀለ የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስትያን አባል ስትሆን: ሶስት የመዝሙር አልበሞችንም ለክርስትያን ወገኖቿ አቅርባለች:: የግል ህይወት ሂሩት በቀለ በሙዚቃ አለም በነበረችበት ጊዜ ከፍተኛ አድናቆትንና ዝናን ያተረፈች እንዲሁም ደግሞ በመንፈሳዊ ህይወቷ ደሰታንና የመንፈስ እርካታን ያገኘች ቢሆንም: የግል ህይወቷን በተመለከተ ግን ያላትን ትርፍ ግዜ ሁሉ ከልጆቿና ከቤተሰቧ ጋር ማሳለፍ እጅግ አድርጎ ያስደስታት ነበር:: ሂሩት ከሙዚቃ ስራዋና ከመንፈሳዊ ህይወቷ በተጨማሪ፥ በጨዋታ አዋቂነቷ በቅርብ የሚያውቋት የስራ ባልደረቦቿ: ጏደኞቿና ቤተሰቦቿ ይናገራሉ:: ሂሩት በቀለ ባደረባት የስኳር ህመም ምክንይት በአገር ውስጥና በውጪ አገር ለረጅም ጊዜ ህክምናዋን ስትከታተል የቆየች ቢሆንም የጌታ ፈቃድ ይፈጸም ዘንድ ግንቦት 4, 2015 ዓ.ም. በተወለደች በ 80 አመቷ ወደምትወደውና ሁሌም ወደምትናፍቀው ወደ የሰማይ አባቷ በክብር ሄዳለች:: ሂሩት በቀለ የ7 ልጆች እናት፣ የ10 ልጆች አያት እና የ7 ልጆች ቅድመ አያት ነበረች። ሂሩት በቀለ በሙያዋ ላበረከተችው አስተዋጽዎ ከአገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ሽልማትና የእውቅና ምስክር ወረቀት ያገኘች ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ለመጥቀስ ያህል: 1ኛ) ከግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ እጅ ከወርቅ የተሰራ የእጅ አምባር እና የምስጋና ደብዳቤ 2ኛ) ከኢትዮጵያ ፖሊስ ሰራዊት ኮሚሽነር የከፍተኛ ስኬትና የላቀ አስተዋጽዎ ሽልማት ከምስክር ወረቀት ጋር 3ኛ) በሙዚቃው ዓለም ላበረከተችው ተሳትፎ ከፖሊስ ሰራዊት ኦርኬስትራ የብር ዋንጫና የምስጋና ደብዳቤ 4ኛ) በሙዚቃው ዘርፍ ለእናት ሐገሯ ላበረከተችው ከፍተኛ አስተዋጽዎ ከቀድሞዎ የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ኮሎኔል መንግስቱ ኃማርያም እጅ ሰርተፍኬት 5ኛ) ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያና በሱዳን ህዝቦች መካከል ያለውን ወዳጅነት ለማደስ ላበረከተችው አስተዋፅኦ የእውቅና የምስክር ወረቀት 6ኛ) ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላበረከተችው የሙዚቃ አስተዋፅዖ ከኢትዮጵያ አብዮታዊ ጦር የፖለቲካ አስተዳደር የምስጋና ደብዳቤና ሽልማት 7ኛ) ከፖሊስ ሰራዊት ኦርኬስትራ የቲያትር እና ሙዚቃ ክፍል የ25-ዓመታት ከፍተኛ ስኬት እና የላቀ አስተዋፅኦ የምስክር ደብዳቤ ከፍተኛ ሽልማት ጋር 8ኛ) ከቀድሞ የሰሜን ኮርያ ፕሬዘዳንት ኪም ኢል ሱንግ እጅ ከወርቅ የተሰራ ሜዳልያ 9ኛ) ከኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነር: ለፖሊስ ሃይል ስፖርት ፌስቲቫል ላበረከተችው አስተዋፅኦ የእውቅና ሰርተፍኬት 10ኛ) ከመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን: ላበረከተችው አስተዋፅኦ ልዩ እውቅና እና የምስጋና ሰርተፍኬት 11ኛ) ከወንጌል ብርሃን አለማቀፍ አገልግሎት ቤተክርስቲያን: በሃይማኖታዊ ህይወት ላሳየችው ትጋትና አስተዋፅኦ የምስጋና ሰርተፍኬት ይገኙበታል 12ኛ) ከጠቅላይ ምንስትር አብይ አህመድ እጅ የህይወት ዘመን ግልጋሎት ሜዳልያ ይገኙበታል የኢትዮጵያ ዘፋኞች
9583
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%88%80
ተረት ሀ
ሀሜተኛ ነው ከዳተኛ ሀሜተኛ ያፍራል ሀስተኛ ይረታል ሀሜት አይቀር ከድሀም ቤት ሀሜትና ጅራት በስተኋላ ነው ሀምሌ ቢያባራ በጋ ይመስላል ሀምሌና ሙሽራ ሳይገለጡ ነው ሀምሌን በብጣሪ ነሀሴን በእንጥርጣሪ ሀምሳ ሎሚ ለሀምሳ ሰው ጌጡ ለአንድ ሰው ሸክሙ ሀረጉን ሲስቡት ዛፉ ይወዛወዛል ሀረጉን ሳብ ዛፉ እንዲሳሳብ ሀረግ ለመዳፍ አልጋ ለምንጣፍ ሀሰተኛ ምስክር ጉልበት ይሰብር ሀሰተኛን ሲረቱ በወንድም በእህቱ ሀሰተኛ ሲናገር ይታወቃል ስሱ ሲበላ ይታነቃል ሀሰተኛ ሲናገር ይታወቃል በሶ ሲበሉት ያንቃል ሀሰተኛ በቃሉ ስደተኛ በቅሉ ሀሰተኛ ብርቱ ወንጀለኛ ሀሰተኛ ያወራውን ፈረሰኛ አይመልሰውም ሀሰት ስለበዛ እውነት ሆነ ዋዛ ሀሰት ቢናገሩ ውቃቢ ይርቃል ሀሰትና ስንቅ እያደረ ያልቅ ሀሰት አያቀላ እውነት አያደላ ሀሰት አያድንም መራቆት መልክ አያሳምርም ሀስት እያደር ይቀላል እውነት እያደር ይበራል ሀስት እያደር ይቀላል እውነትና ውሀ እያደር ይጠራል ሀሰት ነገር ክፉ ገሀነም እሳት ትርፉ ሀሳቡ ጥልቅ ነገሩ ጥብቅ ሀሳብህን ጨርቅ ያድርገው ሀሳብና መንገድ ማለቂያ የለውም ሀሳብ ከውለታ አይቆጠርም ሀሳብ ከፊት አይፈታ ሙት አይመታ ሀሳብ ያገናኛል ፍራት ያሸኛኛል ሀሳብ ያገናኛል ፍርሀት ያሸኛኛል ሀ ሳይሉ ጥፈት ውል ሳይዙ ሙግት ሀ ባሉ ተዝካር በሉ ሀ ባሉ ደሞዝ በሉ ሀብታም ለሀብታም ይጠቃቀሱ ድሀ ለድሀ ይለቃቀሱ ሀብታም ለሰጠ የድሀ ሙርጥ አበጠ ሀብታም ለሰጠ የድሀ ሙርጥ ያብጣል ሀብታም ለሰጠ ደሀ ምንጭሩ አበጠ ሀብታም ለሰጠው ደሀ ይንቀጠቀጣል ሀብታም ሊሰጥ የደሀ ቂጥ ያብጥ ሀብታም ሊሰጥ የደሀው ሙርጥ ያብጣል ሀብታም ሊሰጥ ደሀ ምርጥ ያወጣል ሀብታም ሲወድቅ ከሰገነት ድሀ ሲወድቅ ከመሬት ሀብታም በመመጽወቱ ድሀ በጸሎቱ ሀብታም በከብቱ ድሀ በጉልበቱ ሀብታም በወርቁ ድሀ በጨርቁ ሀብታም በገንዘቡ ድሀ በጥበቡ እርስ በርስ ይቃረቡ ሀብታም በገንዘቡ ይኮራል ድሀ በጥበቡ ይከብራል ሀብታም ቢሰጥ አበደረ እንጂ አልሰጠም ሀብታም ቢያብር ድህነትን ያጠፋል ሀብታም ነው መባል ያኮራል ድሀ ነው መባል ያሳፍራል ሀብታም እንደሚበላለት ድሀ እንደሚከናወንለት ሀብታም ያለ ድሀ አይኮራም ድሀ ያለ ሀብታም አይበላም ሀብታም ገንዘቡን ያስባል ድሀ ቀኑን ይቆጥራል ሀብት እና እውቀት አይገኝ (ም ) አንድነት ሀብት የጠዋት ጤዛ ነው ሀኪም ሲበዛ በሽተኛው ይሞታል ሀኪም የያዘው ነፍስ ባያድር ይውላል ሀኪሞች እስኪመካከሩ በሽተኛው ይሞታል ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ ሀዘንና ደስታ ጎን ለጎን ናቸው ሀዘንን የፈራ በደስታ የተጣራ ሀይለኛ ውሀ አሻቅቦ ይፈሳል ሀይለኛ ዱቄት ከነፋስ ይጣላል ሀይማኖቱ ከጅማት ጉልበቱ ከብረት የጠና ሀይማኖት ከግብር ጸሎት ከፍቅር ሀይማኖት ያለ ፍቅር ጸሎት ያለ ግብር ሀይማኖት የሌለው ሰው ልጓም የሌለው ፈረስ ነው ሀጢአት ለሰሪው ምህረት ለአክባሪው ሀጢአት ሲደጋገም ጽድቅ ይመስላል ሀጢአት ሳያበዙ በጊዜ ይጓዙ ሀጢአት በንስሀ በደል በካሳ ሀጢአት በንስሀ እድፍ በውሀ ሀፍረት ያከሳል ያመነምናል ሁለተኛ ደሞ ለዘበኛ ! አሉ ሁለተኛ ግፌ ጫንቃዬን ተገርፌ ልብሴን መገፈፌ ሁለተኛ ግፍ ልብሴን ይገፍ ጀርባዬን ይገርፍ ሁለተኛ ጥፋት ቆሞ ማንቀላፋት ሁለተኛ ጥፋት ከገበያ ማንቀላፋት ሁለተኛ ጥፋት ከገበያ ቆሞ ማንቀላፋት ሁለቱን የተመኘ አንዱንም አላገኝ ሁለቱን የተመኘ አንድም አላገኘ ሁለቱን ወንበዴ በአንድ ዘዴ ሁለቴ ሰላምታ አንዱ ለነገር ነው ሁለት ሆነው የተናገሩት በመሬት የቀበሩት ሁለት ሞት መጣ ቢለው አንዱን ግባ በለው አለ ሁለት ሞግዚት ያለው ህጻን ያለጥርጥር በእሳት ይቃጠላል ሁለት ቁና ሰጥቼ አንድ ጥንቅል ሁለት ባላ ትከል አንዱ ሲስበር ባንዱ ተንጠልጠል ሁለት ባላ ትከል አንዱ ሲነቀል ካንዱ ተንጠልጠል ሁለት ብልጥ ኑግ አያደቅ ሁለት አይወዱም ከመነኮሱ አይወልዱም ሁለት አይወዱ ከመነኩሴ አይወልዱ ሁለት አይወዱ ከመነኮሱ አይወልዱ ሁለት አገር አራሽ ለባልንጀራው አውራሽ ሁለት እግር አለኝ ብሎ ሁለት ዛፍ አይወጡም ሁለት እግር አለኝ ብሎ እሁለት ዛፍ አይወጣም ሁለት እግር አለኝ ተብሎ ሁለት ዛፍ አይወጣም ሁለት አፎች ባይናከሱ ይናቀሱ ሁለት ወፎች ባይናከሱ ይናቀሱ ሁለት የተመኘ አንድም አላገኘ ሁለት የወደደ አንዱን ሳያገኝ ሄደ ሁለት ጉድጓድ ያላት አይጥ አትሞትም ሁለት ጊዜ ተናገርህ ከፋህ ሁለት ጊዜ በላህ ተፋህ ሁለት ጊዜ ተናግረህ ከፋህ ሁለት ጊዜ በላህ ተፋህ ሁለት ጊዜ ነው የዶሮ ልደት አንዱ በእንቁላል አንዱ በጫጩት ሁለት ጊዜ ይፈርዱ ጉድ ይወልዱ ሁለት ጥፉ ካገር ይጥፉ ሁሉ ሄዶ ተበተነ እህና እኔ ቀረነ አለ እያዘነ ሁሉ ሄደ ተበተነ እህና እኔ ቀረነ አለ ያዘነ ሁሉ ሆነ ቃልቻ ማን ይሸከም ስልቻ ሁሉም ሰው መምሰሉ ባይታይ አመሉ ሁሉም ሸክሙን ፍቅርም ያዥውን ሁሉም በየዘመድህ ቢሉት አክንባሎ ጋጥ ገባ ሁሉም አካል ነው ግን እንደአይን አይሆንም ሁሉም ከኋላው ያገኘዋል እንደስራው ሁሉም ከልኩ አያልፍም ሁሉም ወንፈሉን ፈታይም ድውሩን ሁሉም ያልፋል እውነት ብቻ ይተርፋል ሁሉ በእጄ ሁሉ በደጄ ሁሉ ቢናገር ማን ይሰማል ሁሉ አማረኝን ገበያ አታውጣት ሁሉ አረሰ ማን ይሸምት ሁሉ የሚገኝ ከእሱ የሚገኝ የለም ያለእርሱ ሁሉን ለእኔ አትበል ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል ሁሉን አውቆ አሳውን እሾህ ከስጋው ለይቶ ሁሉ ያልፋል እስኪያልፍ ያለፋል ሁሉም ያልፋል ግን እስኪያልፍ ያለፋል ሁሉ ያልፋል እውነት ብቻ ይተርፋል ሁሉም በየዘርህ ቢሉት አከንባሎ ጋጣ ገባ ሁሉም ያልፋል የሚኮርጅም ቢሆን ሁሉ አማረሽን ዲስኮ () አታውጧት ሁሉ አማረሽን ገበያ አታውጧት ሁል ጊዜ ባሬራ ትበያለሽ ወይ አንዳንድ ጊዜ እንኳ ወጥ አትይሞይ ሁል ጊዜ ከመደንገጥ አንድ ጊዜ መሸጥ ሂዳ ጉበት ቢነሷት ታናሽ ታላቅ ስደዱልኝ አለች ሂዳ ጉበት የነሷት ታናሽ ታላቅ ስደዱልኝ አለች ሂዳ ጉበት ይነሷታል ታናሽ ታላቅ ላኩልኝ አለች ሂድ አትበለው እንዲሄድ አድርገው ሂድ አትበለው እንደሚሄድ አርገው ሂድ ካገር ኑር ካገር ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም ህልም አለ ተብሎ ሳይተኛ አይታደርም ህመሙ ቀርቶ ሞቱን በሰጠኝ ህመሙ ቀርቶ ሞቱን በተወኝ ህመሙን የሸሸገ መድሀኒት የለውም ህመሙን የደበቀ መድሀኒቱም አልታወቀ ህመሙን የደበቀ መድሀኒት የለውም ህዳር መማረሪያ ሰኔ መቃጠሪያ ህያዋን ለነገስታት ሙታን ለካህናት ይገብራሉ ህግ ይኖራል ተተክሎ ስርአት ይኖራል ተዛውሮ ሆሆሆ ስቄ ልሙት አለ ሰውየው ሆቴል ቢያብር ገንዘብ ያስገኛል ሆደ ሰፊ ነገር አሳላፊ ሆደ ሰፊ ይሻላል ከአኩራፊ ሆዱ ሲሞላ ፍቅሩ ሌላ ሆዱ ሲጎድል ሰው ያጋድል ሆዱ ናረት ሙያው ከጅረት ሆዱን የወደደ ማእረጉን የጠላ ሆዱን የወደደ ማእረጉን ይጠላል ሆዱን ያለ ሆዱን ተወጋ ሆዱ ወድዶ አፉ ክዶ ክፉ ለምዶ ሆዱ ፈሪ እግሩ ዳተኛ አዳም ሲዋጋ እርሱ ይተኛ ሆዳም ሰው እንብርት የለውም ሆዳም ቢሸከም የበላ ይመስለዋል ሆዳም ቢፈተፍት የጠገበ ይመስለዋል ሆዳም ፍቅር አያውቅም ሆዴ በጀርባዬ ቢሆን ገፍቶ ገደል በጣለኝ ሆዴ ኑር በዘዴ ሆዴን በልቶኝ ጎኔን ቢያኩኝ አይገባኝ ሆዴ አታጣላኝ ከዘመዴ ሆድህና ልጅህ አይጥሉህ ሆድህን ጎመን ሙላው ጀርባህን ለጠላት አታሳየው ሆዴ ሆዴ የሚለውን ጌታ ያየዋል አይኔ አይኔ የሚለውን ሰው ያየዋል ሆድ ሆዴን የምትል ወፍ አለች ምናለች ሆድ ለማታ በልቶ ለጠዋት ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ሆድ ለባሰው ቢላዋ አታውሰው ሆድ ለተተባሰው ማጭድ አታውሰው ሆድ ሲሞላ ራስ ባዶ ይቀራል ሆድ ሲያር ጥርስ ይስቃል ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ጠዋት ሆድ ባዶን ይጠላል ሆድ ባዶ ይጠላል ሆድ ከሁዳድ ይስፋል ሆድ ካገር ይስፋል ሆድ እንዳሳዩት ነው ሆድና ግንባር አይሸሸጉም ሆድና ግንባር አይሸሸግም ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት ዳገት ላይ ይለግማል ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግማል ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግማል ሆድ ወዶ አፍ ክዶ ክፉ ለምዶ ሆድ ዘመድ ሳይወድ አፍ እህል ሳይለምድ ሆድ የኔ ነው ሲሉት ቁርጠት ሆኖ ይገድላል ሆድ የሸሸገውን ብቅል ያወጣዋል ሆድ ያበላውን ያመሰገናል ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል
44626
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%9B%E1%8B%AD%E1%88%B4
ዛይሴ
ዛይሴ ወይም ዘይሴ በኢትዮጵያ ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል የሚገኝ ብሔረሰብ ነው። የዛይሴ ብሔረሰብ በጋሞ ጎፋ ዞን በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ኤልጎ፣ወዘቃ እና ዛይሴ ደንብሌ በሚባሉ የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ የሚኖር ሲሆን፣እነዚህ ቀበሌዎች ከጋሞጎፋ ዞን ርዕሰ ከተማ አርባ ምንጭ በ22 ኪ.ሜ. ርቀት ውስጥ የሚገኙ ናቸው። ከአርባ ምንጭ ወደ ደቡብ ኦሞ ዞን፣ ኾንሶና ዲራሼ ልዩ ወረዳዎች የሚያቋርጠው አውራ መንገድ የኤልጎንና የወዘቃ ቀበሌዎችን አቋርጦ ያልፋል። ብሔረሰቡ በዋናነት የሰፈረባቸዉ ቀበሌያት የመሬት አቀማመጥ የጫሞ ሐይቅ ዳርቻን የጋሞ ሰንሰለታማ ተራሮችንና የመጨረሻ ጫፍ ኮረብታማ አካባቢን ይዞ የሚገኘውን ለእርሻና ከብት ርቢ ምቹ የሆነ ለም መሬትን ሲያካትት፤የአየር ንብረቱ ደጋ፣ ወይናደጋና ቆላማ ነው። በ1999 ዓ/ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት መሠረት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 17,884 ነው። የብሔረሰቡ አባላት የኢኮኖሚ መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን ለፍጆታና ለገበያ የሚውሉ የተለያዩ ሰብሎችን ያመርታል። በቆላማው የአየር ንብረት ክልል በቆሎ፣ጥጥ፣ ማሽላ፣ ጤፍ፣ ማንጎ፣ አቦካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ፣ ሎሚ ለገቢ ምንጭነት የዝናብን ወቅት በመጠበቅና መስኖ በመጠቀም ያመርታሉ። “ሀለኮ” /ሽፈራው/ የተባለውን ተክል ለምግብነትና ለመድሐኒትነት ተግባር በስፋት ይመረታል። ንብ ማነብ ሌላው የብሔረሰቡ ተግባር ሲሆን ከቤት እንሰሳት የዳልጋ፣ የጋማ ከብቶችንና ፍየሎችን ያረባሉ። ከግብርና በተጨማሪ የዕደ ጥበብ ስራዎችን ለገቢ ምንጭነት ይጠቀሙባቸዋል። የብሔረሰቡ ቋንቋ በብሔረሰቡ አባላት «ዘይሴቴ»ተብሎ ሲጠራ ሌሎች ደግሞ «ዛይሴኛ» ይሉታል። የዛይሴቴ ቋንቋ ከምሥራቅ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ውስጥ የሚመደብ ሲሆን፤ ከጋሞና ከኮሬቲቴ ቋንቋዎች ጋር ይመሳሰላል። ቋንቋው ከመግባቢያነት አልፎ ለሌላ ተግባር አልዋለም። ። ታሪካዊ አመጣጥና አሠፋፈር የብሔረሰቡን ታሪካዊ አመጣጥና አሰፋፈር በተመለከተ በተለያዩ ሕዝቦች አካባቢ በተከሰቱ እንቅስቃሴዎች የተነሣ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ጎሳዎች በፈጠሩት የረጅም ጊዜ ማህበራዊ መስተጋብር የዛይሴን ብሔረሰብ እንዳስገኙ ይነገራል። እነዚህ ጎሣዎች ወደ አካባቢው ለምን እንደተንቀሳቀሱና እንደሰፈሩ በምክንያትነት የሚነገረው አካባቢው ለእርሻና ለከብት ርቢ ምቹ መሬት ለኑሮ ተስማሚ የሆነ የአየር ንብረት ያለው መሆኑ ነው። በብሔረሰቡ በርካታ ጎሣዎች እንዳሉ ሲነገር ከነዚህም መካከል “ቡቡር”፣”ብልዝና” “ማልዝ” ነባር ጎሣዎች ሲሆኑ የተቀሩት ከጋሞ፣ከደራሼ፣ ከሞሲዬና ከኮሬ በተለያዩ ጊዜያት መጥተው የተቀላቀሏቸው መሆኑን የብሔረሰቡ አዛውንቶች ይናገራሉ። ከእነኚህ በተጫማሪም ቀደም ባሉት መንግሥታት በሥራና በሰፈራ ምክንያት ከጋሞ፣ከኮንሶ፣ከዎላይታ፣ከጎፋና ከአማራ የመጡ ሕዝቦች ከብሔረሰቡ ጋር አብረው እንደሚኖሩ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ባህላዊ አስተዳደር ዘይሴዎች የራሣቸው የሆነ ጥንታዊ ባህላዊ አስተዳደር አላቸው። የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮ «ካቲ» ወይም ንጉሱ ይባላል፡፤ ካቲዎች የሚነግሱት አመጣጡ ከጋሞ-ኮሌ አካባቢ “ዝሄ” ከሚባል ሥፍራ “ከዙሌሣ” ጎሣ ነው። የካቲው ሥልጣን የዘር ሀረግን ተከትሎ ከአባት ወደ ልጅ በውርስ የሚተላለፍ ሲሆን ለመሪነት የሚያበቃው ገና ሲወለድ የእህል ዘር፣ እርጥብ ሣር ወይም የከብት እበት ይዞ ከእናቱ ማህፀን የሚወጣው ወንድ ልጅ ነው ተብሎ ይነገራል። ይህም በባህሉ “ኤቃ” ወይም /ገዳም/ የመልካም ገድ ተምሳሌት ነው ተብሎ ይታመናል። ከካቲው ልጆች መከካከል የመጨረሻ ወይም ታናሽ እንኳን ቢሆን ከኤቃ ጋር ከተወለደ የካቲው ወራሽ የሚሆነው እርሱ ይሆናል። ወራሽ ልጅ መሪው ወይም ካቲው በሕይወት እስካለ ድረስ ከአባትየው ርቆ እንዲኖር ይደረጋል። ለዚህም በምክኒያትነት የሚጠቀሰው ወራሹ ከአባቱ ጋር ከኖረ ለአባትየው ሕይወት አስጊ ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው። ከባህላዊ መሪው በታች አቻ ሥልጣን ያላቸው በሕዝብ የሚመረጡ «ማጋ» የተባሉ ሰባት የሕዝብ መሪዎች አሉ። የማጋዎቹ ሥልጣንም እንደ ካቲው ሁሉ የዘር ሐረግን ተከትሎ ከአባት ወደ ልጅ የሚተላለፍ ነው። ከማጋዎች ቀጥለው የሚገኙት የሥልጣን አካላት «ሶሮፋዎች» ሲባሉ ዋና ተግባራቸው ለበላይ መሪዎች የማማከር አገልግሎት መስጠት ነው። የሚመረጡትም በሕዝብ ሸንጎ ነው። በወታደራዊ አመራር ረገድ “ቶራ ቃራ” የሚባሉ የጦር አዛዦች እንደነበሩ ይነገራል። እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ባህላዊ አስተዳደር አካላት በአስተዳደሩ ማዕከል በሆነው “ማርታ” /ቤተመንግሥት/ ዙሪያ በመሰባሰብ የፖለቲካ አስተዳደሩን ይመሩ ነበር። ንጉሡ የራሱ የጦር ሠራዊት አለው። በዚህ ጦር ውስጥ ዕድሜው 18 ዓመት የሞላው ወጣት ለካቲው ይሰጥና ወታደራዊ ሥልጠና ይወሰዳል። ከሥልጠናው መልስ ምሽግ በመቆፈር አካባቢውን በመጠበቅ ወታደራዊ ግዴታውን የመወጣት ኃላፊነት ይሰጠዋል። በባህላዊ አስተዳደሩ የሴቶች ተሣትፎ ዝቅተኛ ነው። በቤትና በሸንጎ የመስተንግዶ ስራን ከመምራት ውጪ የመዳኘት መብት የላቸውም። ይሁንና የካቲው ሚስት ባሏን በማማከር ትረዳዋለች። የሴቶች ምክርና ግሣፄ ይደመጣል። ምክንያቱም ግሣፄዋን የጣሰ ያሰበው አይሳካለትም ወይም አይሟላለትም ተብሎ ስለሚታመን ነው። በሌላ በኩል ከአጎራባች ሕዝቦች ጋር አለመግባባት ሲከሰት “ኦጌማጋ” በሚባል አገናኝ አማካይነት በመላላክ “ዱላታ” /የሕዝብ ሸንጎ/ ተካሂዶ የዕርቅ ሥርዓት ይፈፀማል። ጉዳዩ ጠንከር ያለ ከሆነ በካቲውና በማጋዎች አማካይነት በውይይትና በሰላማዊ መንገድ ይፈታል። በዚህም የተነሣ የዛይሴ ብሔረሰብ ከአጎራባች ብሔረሰቦች ጋር በርካታ ባህላዊ ጉዳዮችን ይጋራል። በአስተራረስ፣ በአለባበስ በሰርግና በለቅሶ ስርዓት አፈጻፀምና በሌሎችም ባህላዊ ወጎች ተመሣሣይነት አለው። ይሁንና ብሔረሰቡ ራሱን በራሱ ሲያስተዳድር ከነበረበት የቀድሞ ሁኔታ በውጫዊ ተጽዕኖዎች ምክንያት ባህላዊ አስተዳደርሩም ሆነ ሌሎች ባህላዊ ዕሴቶቹ መዳከማቸው አልቀረም። በባህላዊ ሥርዓቱ ላይ ጫና ከፈጠሩበት ዓቢይ ምክንያቶች የአፄ ምኒልክ የመስፋፋት ዘመቻ እና የጣሊያን ወረራ ለአብነት ተጠቃሽ ናቸው። ባህላዊ ዕሴቶች የጋብቻ ሥርዓት በብሔረሰቡ የጋብቻ ሥርዓት የሚፈፀመው በአቻ ጎሣዎች መካከል ነዉ። በአንድ ጎሣ ውስጥ የሚመደቡ እርስ በርስ ጋብቻ አይፈፅሙም። በብሔረሰቡ ባሕል ሴቶች ፈፅሞ አይገረዙም፣ ወንዶች አልፎ አልፎ በስለት ወይም ቆንጨኮ /ወተት የሚወጣውን ተክል/ በመጠቀም ግርዛት ይፈፀማሉ። ለጥሎሽ ጥንት በዓይነት እስከ ሰባት ከብት፣ ለልጅቱ ወላጆችና ቤተዘመድ ይከፈል ነበር። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የጥሎሹ መጠን በጥሬ ገንዘብ ከ1,000-2,000 ብር እንደደረሰ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የበዓላት አከባበር ብሔረሰቡ ከሚያከብራቸው መንፈሳዊና ባህላዊ በዓላት “ደሴከሶ”፣”ኤቃ”፣”አልሶ”፣” መስቀል”፣ “ገና” የተባሉት ተጠቃሽ ናቸዉ። ደሴ ከሶ (የእኩያሞች በዓል) በተመሣሣይ የዕድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ወጣቶች በአማካይ ሥፍራ ተሰብስበው የብሔረሰቡ ባህል ወግና ታሪክ ለወጣቶች በብሔረሰቡ አዛውንቶች እየተተረከና እየተወሳላቸው እነርሱም የታሪክ ተረካቢ መሆናቸው እየተገለፀላቸው ለክብረ ባዕሉ በተዘጋጀው ድግስ ታድመው በጋራ እየበሉና እየተጫወቱ በአገሬው ሽማግሌዎች ተባርከውና ተመርቀው የአንድ ትዉልድ ስያሜ የሚያገኙበት በዓል ነው። ኤቃ /መስዋዕት የማቅረቢያ በዓል/ በዚህ የብሔረሰቡ ሃይማኖታዊ በዓል “ማጋዎች” ለአካባቢያቸው ሰላምና ብልፅግናን በመሻት ፈጣሪአቸው “ኢንአ”/ማካ/ በሚባሉ የባህላዊው ሥርዓተ አምልኮ ፈፃሚዎች አማካይነት ለብሔረሰቡ አምልኮት መስዋዕት በማቅረብ ፀሎት የሚያቀርቡበት ሥርዓት ነው። አልሶ በአካባቢው አሉታዊ ተፈጥሮአዊ ክስተቶች /ድርቅ፣የአንበጣ መንጋ ወረርሽኝ፣ ወዘተ... /ሲከሰት ከዚህ መቅሰፍት እንዲታደጋቸው ካቲውና ማጋዎች በፀሎትና በምልጃ ለፈጣሪያቸው መስዋዕት የሚያቀርቡበት ሥርዓት ነው። የመስቀል በዓል፡- ካቲውና ማጋዎች ለበዓሉ ተለይቶ በተዘጋጀ ሥፍራ ደመራ ደምረው ችቦ በማቀጣጠል የአካባቢው ሕዝብ እየበላና እየጠጣ በጭፈራ የሚያከብረው በዓል ነው። ከዚህ በተጨማሪም ከክርስትና እምነት ጋር በተያያዘ የገናና የፋሲካ በዓላት በአካባቢው ብሔረሰብ በድምቀት ያከበራሉ። ባህላዊ ጨዋታዎች በባህላዊ ጨዋታዎች ረገድ ሴቶችና ወንዶች በአንድነት ተሰባስበው ሴቶቹ በስነ ቃል ጎሣቸውን ሲያሞጋግሱ ወንዶች በጭብጨባና በክራር በታገዘ እንቅስቃሴ ሽቅብ እየዘለሉ ይጨፍራሉ። ከሙዚቃ መሣሪያዎች ዋሽንት (ሱልንጌ) ክራር/ዝንቤ/፣ ዛዬ የትንፋሽ መሣሪያ በራሣቸው ጥበብ በመሥራት ደስታቸውንና ሃዘናቸውን በሚገልጹበት ወቅት በማጀቢያነት ይጠቀሙባቸዋል። የዘመን አቆጣጠር ብሔረሰቡ የራሱ የሆነ የቀን፣ የወርና የዓመት አቆጣጠር አለው። የሰባት ቀናትና የአሥራ ሁለት ወራት የራሣቸው መጠሪያ ሲኖራቸው ወቅቶችንም ከሐምሌ - ሕዳር “ሴቴ”፣ ከታህሣሥ - የካቲት “ቦኔ”፣ ከመጋቢት - ሰኔ “ባርጎ” በሚል ስያሜ ከፋፍለው ይጠሯቸዋል። ባህላዊ የቤት አሰራር ዛይሴዎች ሰፋ ያለ ዝግጅት በማድረግ ባለሦስት ማዕዘን ግድግዳ ቤታቸውን በአበሻ ፅድ በመገርገድና ጣሪያውን በጠንካራ ሰንበሌጥ በመክደን ይሠሩታል። ሣሩ በእበትና በጭቃ ስለሚነከር እሣት ቢነሳ እንኳን የመቋቋም ኃይል አለው። የቤቱን ጣራ ብዙውን ጊዜ ከስምንት እስከ አሥራ ሁለት በሚሆን የጥድና የወይራ ምሰሶዎች ከውስጥ ወደ ዉጪ በመወጠር ያቆሙታል። ዘይሴዎች የቤት ቁሣቁሦችን፣የእርሻ እና የሙዚቃ መሣሪያዎችን እንዲሁም ሌሎች መገልገያዎችን በባህላዊ መንገድ ሠርቶ የመጠቀም ባህል አላቸው። የሽመና ውጤት የሆኑትን ቡልኮ፣ጋቢ፣ ነጠላና ቆልኤ ከጥጥ ያዘጋጃሉ። የእርሻ መሣሪያዎችን ከእንጨትና ከብረት በመሥራት ሲገለገሉ ገበቴ/ጎንጌ/ ፣ሾርቃ(ሀሌ)፣ አርሣ(አልጋ)፣ መቀመጫ (ጽጎ) የተለፋ የቆዳ ምንጣፍ /ሽሬ/ ከተለያዩ ከአካባቢው ከሚያገኝዋቸው ቁሳቁሶች በመሥራት ይገለገሉባቸዋል። ባህላዊ አመጋገብ ዛይሴዎች ባህላዊ ምግባቸውን ከተለያዩ የእህል ዓይነቶችና ከእንሰት ተዋፅኦ በማዘጋጀት ይመገባሉ። ወተት ቅቤና ማርን ለማባያነት ይጠቀማሉ። ባህላዊ መጠጣቸው ቦርዴ/መዶ/ ሲሆን የሚዘጋጀውም በቆሎ፣ማሽላ፣ጎመንና ቆጮን በመደባለቅ እና በመቀላቀል ደልዋዴ የተባለ እርሾ በማዘጋጀት ነው። ከዚያም ከተለያዩ የእህል ዓይነቶች ሰጋለ የሚባል ደፍድፍ ተዘጋጅቶ ከእርሾው ጋር በማዋሃድ በውሃ እየተበጠበጠ ይጠጣል። ከባህላዊ ምግባቸው ቂጣ/ቦራ/ ፣ሱልአ (ከጎመንና ከበቆሎ ዱቄት በመደባላቅ የሚሠራ) ቆዴ -(ከገብስ፣ከበቆሎና ከቡላ ዱቄት የሚሠራ) ገንፎ እና ባምኤ (-ከቦቆሎና ማሽላ ዱቄት የሚሠራ ኩርኩርፋ) ዋንኞቹ ናቸው። ባህላዊ አለባበስ ዘይሴዎች ከእድሜ እና ከፆታ አንፃር የተለያየ የአለባበስ ስርዓት አላቸው። ሕፃናት በእጅ የተሰፋ አቡጀዲ በአንገታቸው ይታሠርላቸዋል። በወጣትነት የዕድሜ ክልል የሚገኙት ደግሞ ሰፋ ያለ ቁምጣ ሱሪ ይታጠቃሉ። ሴቶች ከጥጥ ፈትል የተሠራ ቀሚስና ነጠላ ይለብሣሉ። በተጫማሪም ወፈር ያለ ነጠላ፤ ጋቢ ከወገባቸው በታች ሽንሽን እንዲኖረው አድርጐ በማሰር “ዳንጮ” በተባለ መቀነት ወገባቸው ላይ ሸብ አድርገው ይለብሳሉ። አዛዉንቶች ደግሞ ሰፋ ያለ ቁምጣ፣እጀ ጠባብ ሸሚዝና ኮት ለብሰው ከላይ ጋቢ ወይም ቡልኮ ይደርባሉ። ባህላዊ መሪዎች አለባበሣቸው ከአዛውንቶች ተመሣሣይ ሆኖ ለክብራቸው መለያነት ደበሎ የተባለውን ከአውሬ ቆዳ ተለፍቶና አምሮ የተሠራ መላባሻ ከላይ ይደርባሉ።በእጃቸው ደግሞ ጭራ ይይዛሉ። የለቅሶና የሐዘን ሥርዓት የዛይሴ ብሔረሰቡ የለቅሶና የሃዘን ሥርዓት እንደሟቹ የዕድሜ ክልል፣ እንዳላቸው የሀብት መጠንና የሥልጣን ደረጃ ይለያያል። ለህፃናት ሞት ብዙም አይለቀስም። ሃዘኑ መሪር የሚሆነው ወጣቶች ሲሞቱ ነው። ወጣት ሲሞት ቤተሰቦችና የቅርብ ዘመዶቹ በለጋ ዕድሜው መቀጨቱን በሥነ ቃል እየገለፁ በስለት ግንባርንና ፊታቸውን በመቧጨር እየዘለሉ በመውደቅና በመፈጥፈጥ እንዲሁም የሟችን ንብረት በማውደም ሃዘናቸውን ይገልፃሉ። በዕድሜ የገፋ ሰው ሲሞት ለቅሶው ቀልድና ጨዋታ በተቀላቀለበት መልኩ ይፈፀማል። ካቲው/መሪው/ ሲሞት ሕዝቡ ለለቅሶው ሥርዓት አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ መልዕክት እንዲያስተላልፉ ለማጋዎች ይላካል። ለካቲዎች «ጋሬ» የሚባል ለየት ያለ የለቅሶና የሃዘን ሥርዓት ይደረግላቸዋል። በቅድሚያ በማጋዎች አማካይነት የካቲው ሞት በአዋጅ ለሕዝብ ይነገራል።የካቲውን የቀብር ሥርዓት የሚፈፅሙት "ኢናማካ" በሚል ስያሜ የሚታወቁ ጐሣዎች ናቸው።የግብዓተ መሬት ከተፈፀመ በኋላ ጉድጓዱ የሚሞላው በአፈር ሣይሆን በጥሬ እህል ነው። የካቲው ለቅሶና ሐዘን ከ15-30 ቀናትን ይወስዳል። በካቲው ሞት የተሰማቸውን መሪር ሃዘን ለመግለፅ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ቅንድባቸዉንና ፀጉራቸውን ይላጫሉ። አመድ፣ጥላሸትና ጭቃ ይቀባሉ። እርጉዝ ሴት ደግሞ በሆዷ ላይ ጭቃ ትቀባለች። ይህም በሆዷ የያዘችው ፅንስ ጭምር ሀዘኑን ለመሪው እንዲገልፅለት በሚል እምነት ነው። በዚህ የለቅሶ ስርዓት የብሔረሰቡ አባላት “ጋይሎ” በሚባል ሥነ ቃል ሟች በህይወት ዘመኑ የፈጸማቸውን ጀብዶችና ገድሎች እያነሱ በዜማ በማወደስ ሐዘናቸውን የሚገልጹበት መንገድ ነው። ዋቢ ምንጭ ዛይሴ ብሔረሰብ የኢትዮጵያ ብሔሮች
11265
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%80%E1%88%9D%20%E1%88%8A%E1%8A%95%E1%8A%A8%E1%8A%95
አብርሀም ሊንከን
አብርሀም ሊንከን (እንግሊዝኛ፦ ፣ የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ የኖሩ) ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፴፰ ዓ.ም. የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጄምስ ፖልክ በሜክሲኮ ላይ ጦርነት ባደረገ ጊዜ አብርሀም ሊንከን የዚህን ጦርነት ተቃዋሚ ነበሩ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና አጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። ይህም የሆነ የሕዝቡ ብዛት በአገሩ ስሜን እየኖረ የሬፑብሊካን ደጋፊዎች ነበሩ። በስሜኑ ክፍላገሮች ደግሞ፣ ባርነት ከዚህ በፊት ተክለክሎ ነበር። በአሜሪካ ደቡብ በተገኙ ክፍላገሮች ግን ባርነት ገና የተለመደ ከመሆኑ በላይ በጥጥ የተመሠረተው የምጣኔ ሀብታቸው አስፈላጊነት መሰላቸው። ስለዚህ የባርነት ተቃዋሚ ሊንከን ፕሬዚዳንት መሆኑ በደቡብ ያሉት ክፍላገሮች ከአሜሪካ መገንጠላቸው ማለት ነበር። እንዲሁም ከምርጫው ቶሎ ተቀጥሎ ማዕረጉንም እንኳን ገና ሳይይዙ፣ ሳውዝ ካሮላይና በታኅሣሥ ፲፪ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. መገንጠሏን አወጀች። በጥቂት ጊዜ ውስጥ ሌሎች የደቡብ ክፍላገሮች እንዲህ አዋጁና በጥር ፳፭ ቀን ቴክሳስ ፯ኛው ሆነ። ከዚያ ቀጥሎ እነዚህ ፯ ክፍላገሮች በሞንትጎመሪ፣ አላባማ ተባብረው አዲሱ መንግሥት የአሜሪካ ኮንፌዴራት ክፍላገሮች () ተባሉ። በየካቲት ፳፮ ቀን ሊንከን የፕሬዚዳንትነቱን ማዕረግ በተቀበሉበት ቀን አገሩ በተግባር በሁለት ተከፋፍሎ ነበር። የደቡብ ፕሬዚዳንት ጄፈርሰን ዴቪስ ሆኑ። የደቡብ ክፍላገሮች ለጦርነት ተዘጋጁና ምሽጎች ከ ሠራዊት ሊይዙ ጀመር። በሚያዝያ ፭ ቀን ፎርት ሰምተር ምሽግ በሳውስ ካሮላይና በግፍ ስለ ተያዘ ጦርነቱ ጀመረ። ስለዚህ ሊንከን ከስሜኑ ፸፭ ሺ ሰዎች ለዘመቻ ጠሩ። ከዚህ በኋላ ሌላ አራት ደቡብ ክፍላገሮች ተገንጥለው ለ ተጨመሩ። የደቡብ ዋና ከተማ ለዋሺንግተን ዲሲ ቅርብ ወደ ሆነው ወደ ሪችሞንድ፣ ቪርጂንያ ተዛወረ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። ቤተሰብ እና ልጅነት አብርሀም ሊንከን የተወለደው እ.ኤ.አ. የካቲት 12፣ 1809 (አውሮፓዊ)፣ የቶማስ ሊንከን እና ናንሲ ሀንክስ ሊንከን ሁለተኛ ልጅ፣ በሆድገንቪል፣ ኬንታኪ አቅራቢያ በሚገኘው ሲንኪንግ ስፕሪንግ ፋርም ውስጥ ባለው የእንጨት ጎጆ ውስጥ ነው። እሱ የሳሙኤል ሊንከን ዘር ነበር፣ ከ፣ ፣ ወደ ስሙ ሂንግሃም፣ ማሳቹሴትስ፣ በ1638 የፈለሰው እንግሊዛዊ ነው። ከዚያም ቤተሰቡ በኒው ጀርሲ፣ ፔንስልቬንያ እና ቨርጂኒያ አልፈው ወደ ምዕራብ ፈለሱ። የሊንከን አባታዊ አያቶች፣ ስሙ ካፒቴን አብርሃም ሊንከን እና ሚስቱ ቤርሳቤህ (እናቴ ሄሪንግ) ቤተሰቡን ከቨርጂኒያ ወደ ጀፈርሰን ካውንቲ ኬንታኪ አዛወሩ። ካፒቴኑ የተገደለው በ1786 የህንድ ወረራ ሲሆን (አውሮፓዊ) የአብርሃም አባት የስምንት አመት ልጅ ቶማስን ጨምሮ ልጆቹ ጥቃቱን አይተዋል። ቶማስ በ1800ዎቹ መጀመሪያ ላይ ቤተሰቡ በሃርዲን ካውንቲ ኬንታኪ ከመስፈራቸው በፊት በኬንታኪ እና ቴነሲ ውስጥ ያልተለመዱ ስራዎችን ሰርቷል። የሊንከን እናት ናንሲ ቅርስ እስካሁን ግልፅ አይደለም፣ነገር ግን የሉሲ ሀንክስ ልጅ እንደነበረች በሰፊው ይገመታል። ቶማስ እና ናንሲ ሰኔ 12፣ 1806 (አውሮፓዊ) በዋሽንግተን ካውንቲ ተጋቡ እና ወደ ኤልዛቤትታውን ኬንታኪ ተዛወሩ። ሦስት ልጆች ነበሯቸው፡ ሳራ፣ አብርሃም እና ቶማስ በሕፃንነቱ የሞተው። ቶማስ ሊንከን በንብረት ይዞታ ምክንያት በፍርድ ቤት ክርክር ከ200 ኤከር (81 ሄክታር) በስተቀር ሁሉንም ከማጣቱ በፊት በኬንታኪ እርሻዎችን ገዝቶ አከራይቷል። በ 1816 ቤተሰቡ ወደ ኢንዲያና ተዛወረ የመሬት ቅየሳ እና የማዕረግ ስሞች ይበልጥ አስተማማኝ ነበሩ. ኢንዲያና "ነጻ" (የባሪያ ያልሆነ) ግዛት ነበረች እና እነሱ በኢንዲያና በፔሪ ካውንቲ ሀሪኬን ውስጥ "ያልተሰበረ ጫካ" ውስጥ መኖር ጀመሩ። እ.ኤ.አ. በ 1860 ሊንከን ቤተሰቡ ወደ ኢንዲያና የሄደው “በከፊሉ በባርነት ምክንያት” እንደሆነ ተናግሯል ፣ ግን በዋነኝነት በመሬት ባለቤትነት ችግር። በስፔንሰር ካውንቲ ኢንዲያና ውስጥ ሊንከን ያደገበት የእርሻ ቦታ በኬንታኪ እና ኢንዲያና፣ ቶማስ ገበሬ፣ ካቢኔ ሰሪ እና አናጺ ሆኖ ሰርቷል። በተለያዩ ጊዜያት የእርሻ፣ የከብት እርባታ እና የከተማ ዕጣ ነበረው፣ ግብር ይከፍላል፣ በዳኞች ላይ ተቀምጧል፣ ርስቶችን ይገመግማል እና በካውንቲ ፓትሮል ውስጥ አገልግሏል። ቶማስ እና ናንሲ አልኮልን፣ ጭፈራን እና ባርነትን የሚከለክል የተለየ ባፕቲስቶች ቤተክርስቲያን አባላት ነበሩ። የፋይናንስ ተግዳሮቶችን በማሸነፍ፣ ቶማስ በ1827 ኢንዲያና ውስጥ 80 ኤከር (32 ሄክታር) የትንሽ እርግብ ክሪክ ማህበረሰብ በሆነው አካባቢ ግልጽ የሆነ ርዕስ አገኘ የእናት ሞት እ.ኤ.አ. ኦክቶበር 5፣ 1818 ናንሲ ሊንከን በወተት ህመም ተሸነፈ፣ የ11 ዓመቷ ሳራ አባቷን፣ የ9 ዓመቱን አብርሃምን እና የናንሲ የ19 ዓመቷን ወላጅ አልባ የአጎት ልጅ ዴኒስ ሃንክስን ጨምሮ የቤተሰብ አስተዳዳሪን ትተዋለች። ከአሥር ዓመታት በኋላ፣ ጥር 20 ቀን 1828፣ ሳራ የሞተ ወንድ ልጅ ስትወልድ ሞተ፣ ሊንከንን አውድሟል። ታኅሣሥ 2፣ 1819፣ ቶማስ ከኤሊዛቤትታውን፣ ኬንታኪ የምትኖረውን መበለት ሳራ ቡሽ ጆንስተንን፣ የራሷን ሦስት ልጆች አገባ። አብርሃም ከእንጀራ እናቱ ጋር ተጠግቶ "እናት" ብሎ ጠራት። ሊንከን ከእርሻ ሕይወት ጋር የተያያዘውን ከባድ የጉልበት ሥራ አልወደደም. ቤተሰቦቹ እንኳን “በንባብ፣ በመፃፍ፣ በመፃፍ፣ በመፃፍ፣ በመፃፍ፣ በግጥም በመፃፍ፣ ወዘተ” ሁሉ ሰነፍ ነበር አሉ። የእንጀራ እናቱ “በአካላዊ ጉልበት” እንደማይደሰት ተናግራለች ነገር ግን ማንበብ ይወድ ነበር። ትምህርት እና ወደ ኢሊኖይ ይሂዱ ሊንከን በአብዛኛው ራሱን የተማረ ነበር። መደበኛ ትምህርቱ የተጓዥ አስተማሪዎች ነበር። በሰባት ዓመቱ ማንበብ የተማረበት ነገር ግን መፃፍ ያልቻለበት በኬንታኪ ሁለት አጫጭር ቆይታዎችን ያካተተ ሲሆን ኢንዲያና ውስጥ በእርሻ ሥራ ምክንያት አልፎ አልፎ ወደ ትምህርት ቤት በሄደበት በአጠቃላይ ከ12 ወራት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ዕድሜው 15. እንደ ጎበዝ አንባቢ ሆኖ ጸንቷል እናም የዕድሜ ልክ የመማር ፍላጎት ነበረው። ቤተሰብ፣ ጎረቤቶች እና አብረውት የሚማሩት ንባባቸው የኪንግ ጀምስ ባይብልን፣ የኤሶፕ ተረት፣ የጆን ቡኒያን ዘ ፒልግሪም ግስጋሴ፣ የዳንኤል ዴፎ ሮቢንሰን ክሩሶ እና የቤንጃሚን ፍራንክሊን የህይወት ታሪክን እንደሚያካትት አስታውሰዋል። በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ እያለ ሊንከን ለቤት ውስጥ ሥራዎች ኃላፊነቱን ወስዶ 21 ዓመት እስኪሆነው ድረስ አባቱን ከቤት ውጭ ከሥራ የሚያገኘውን ገቢ ሁሉ ይሰጥ ነበር። በወጣትነቱ ንቁ ተዋጊ ነበር እና በከባድ መያዝ-እንደ-መያዝ-ካን ዘይቤ (እንዲሁም ካች ሬስሊንግ በመባልም ይታወቃል) የሰለጠኑ። በ21 አመቱ የካውንቲ የትግል ሻምፒዮን ሆነ።"የክላሪ ግሮቭ ቦይስ" በመባል ከሚታወቀው የሩፊያ መሪ ጋር በተካሄደ የትግል ውድድር አሸንፎ በጥንካሬ እና በድፍረት መልካም ስም አትርፏል። በማርች 1830 ሌላ የወተት በሽታ መከሰቱን በመፍራት፣ አብርሃምን ጨምሮ በርካታ የሊንከን ቤተሰብ አባላት ወደ ምዕራብ ወደ ኢሊኖይ ተዛወሩ፣ እና በማኮን ካውንቲ ሰፈሩ። ከዚያም አብርሃም ከቶማስ በጣም እየራቀ መጣ፣በከፊሉ በአባቱ የትምህርት እጥረት። እ.ኤ.አ. በ1831፣ ቶማስ እና ሌሎች ቤተሰቦች በኮልስ ካውንቲ፣ ኢሊኖይ ውስጥ ወደሚገኝ አዲስ መኖሪያ ቤት ለመዛወር ሲዘጋጁ፣ አብርሃም በራሱ ላይ መታ። ቤቱን በኒው ሳሌም ኢሊኖይ ለስድስት ዓመታት ሠራ። ሊንከን እና አንዳንድ ጓደኞቹ ዕቃቸውን በጠፍጣፋ ጀልባ ወደ ኒው ኦርሊንስ፣ ሉዊዚያና ወሰዱ፣ እሱም በመጀመሪያ ለባርነት ተጋልጧል። እ.ኤ.አ. በ 1865 ሊንከን የንግግር ችሎታውን እንዴት ማግኘት እንደቻለ ተጠየቀ ። በህግ አሰራር ውስጥ "ማሳየት" የሚለውን ቃል በተደጋጋሚ ያጋጥመው ነበር ነገር ግን ስለ ቃሉ በቂ ግንዛቤ እንደሌለው መለሰ. ስለዚህ፣ “በዓይን ሲታይ በ6ቱ የኢውክሊድ መጽሃፎች ውስጥ ማንኛውንም ሀሳብ መስጠት እስኪችል ድረስ” እስኪያጠና ድረስ ስፕሪንግፊልድን ለቆ ወደ አባቱ ቤት ሄደ። ጋብቻ እና ልጆች የሊንከን የመጀመሪያ የፍቅር ፍላጎት ወደ ኒው ሳሌም ሲዛወር ያገኘችው አን ሩትሌጅ ነበረች። እ.ኤ.አ. በ 1835 ግንኙነት ውስጥ ነበሩ ነገር ግን በመደበኛነት አልተሳተፉም ። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 25 ቀን 1835 በታይፎይድ ትኩሳት ሞተች። በ1830ዎቹ መጀመሪያ ላይ ከኬንታኪ ሜሪ ኦውንስን አገኘ። እ.ኤ.አ. በ1836 መገባደጃ ላይ ሊንከን ወደ ኒው ሳሌም ከተመለሰች ከኦዌንስ ጋር ለመወዳደር ተስማማ። ኦወንስ በዚያ ህዳር ደረሰ እና ለተወሰነ ጊዜ እሷን ለፍርድ; ሆኖም ሁለቱም ሁለተኛ ሀሳብ ነበራቸው። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 16 ቀን 1837 ኦውንስ ግንኙነቱን ካቋረጠ እንደማይወቅሳት የሚገልጽ ደብዳቤ ጻፈ እና ምንም ምላሽ አልሰጠችም። እ.ኤ.አ. በ1839 ሊንከን ከሜሪ ቶድ ጋር በስፕሪንግፊልድ፣ ኢሊኖይ ተገናኘ፣ እና በሚቀጥለው አመት ታጩ። እሷ የሮበርት ስሚዝ ቶድ ልጅ ነበረች፣ ሀብታም ጠበቃ እና በሌክሲንግተን፣ ኬንታኪ ውስጥ ነጋዴ። በጥር 1, 1841 የተደረገ ሰርግ በሊንከን ጥያቄ ተሰርዟል ነገር ግን ታረቁ እና በ ህዳር 4, 1842 በማርያም እህት ስፕሪንግፊልድ መኖሪያ ውስጥ ተጋቡ። ለሠርግ ሥነ ሥርዓት በጭንቀት እየተዘጋጀ ሳለ ወዴት እንደሚሄድ ተጠይቀው "ወደ ገሃነም እንደማስበው" ሲል መለሰ. እ.ኤ.አ. በ 1844 ባልና ሚስቱ በሕግ ቢሮ አቅራቢያ በስፕሪንግፊልድ ቤት ገዙ ። ማርያም በተቀጠረችና በዘመድ እርዳታ ቤቷን ትጠብቅ ነበር። ሊንከን አፍቃሪ ባል እና የአራት ወንዶች ልጆች አባት ነበር፣ ምንም እንኳን ስራው በየጊዜው ከቤት ይርቀው ነበር። አንጋፋው ሮበርት ቶድ ሊንከን በ1843 የተወለደ ሲሆን እስከ ጉልምስና ድረስ የኖረ ብቸኛ ልጅ ነበር። በ 1846 የተወለደው ኤድዋርድ ቤከር ሊንከን (ኤዲ) በየካቲት 1, 1850 በሳንባ ነቀርሳ ምክንያት ሞተ. ሦስተኛው የሊንከን ልጅ "ዊሊ" ሊንከን የተወለደው ታኅሣሥ 21, 1850 ሲሆን የካቲት 20 ቀን 1862 በዋይት ሀውስ በሙቀት ሞተ። ትንሹ ቶማስ "ታድ" ሊንከን ሚያዝያ 4, 1853 ተወለደ እና ተረፈ. አባቱ ግን በልብ ድካም በ18 አመቱ ሞተ ሐምሌ 16 ቀን 1871 ሊንከን "በሚገርም ሁኔታ ህጻናትን ይወድ ነበር" እና ሊንኮኖች ከራሳቸው ጋር ጥብቅ እንደሆኑ አይቆጠሩም ነበር. እንደ እውነቱ ከሆነ የሊንከን የህግ አጋር ዊልያም ኤች ሄርንዶን ይበሳጫል. ሊንከን ልጆቹን ወደ ህግ ቢሮ ሲያመጣ። አባታቸው የልጆቹን ባህሪ ሳያስተውል በስራው ብዙ ጊዜ የተጠመቀ ይመስላል። ሄርንዶን እንዲህ ሲል ተናግሯል፣ "ትንንሽ አንገቶቻቸውን ለመጠቅለል እንደፈለኩ ብዙ እና ብዙ ጊዜ ተሰምቶኛል፣ ነገር ግን ለሊንከን አክብሮት ስላለኝ አፌን ዘጋሁት። ሊንከን ልጆቹ የሚያደርጉትን ወይም የሚያደርጉትን አላስተዋሉም ነበር።" የልጆቻቸው የኤዲ እና የዊሊ ሞት በሁለቱም ወላጆች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል። ሊንከን በ"ሜላኖሊ" ተሠቃይቷል, ይህ ሁኔታ አሁን ክሊኒካዊ ድብርት ነው ተብሎ ይታሰባል. በኋለኛው ህይወቷ፣ ሜሪ ባሏንና ወንድ ልጆቿን በሞት በማጣቷ ውጥረት ውስጥ ትታገል ነበር፣ እናም ሮበርት በ1875 ለተወሰነ ጊዜ ጥገኝነት እንድትሰጥ አስገደዳት። የአሜሪካ መሪዎች
3371
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8B%E1%88%9D%E1%89%A4%E1%88%8B%20%28%E1%8A%A8%E1%89%B0%E1%88%9B%29
ጋምቤላ (ከተማ)
ጋምቤላ በምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የጋምቤላ ክልል ዋና ከተማ ናት። በላቲቱድና በሎንጂቱድ ላይ ትገኛለች። በ1998 የማዕከላዊ የስታትስቲክ ትመና መሰረት የ31,282 ሰዎች መኖሪያ ስትሆን ከነሱም መሃከል 16,163 ወንዶችና 15,119 ሴቶች ይገኙባታል። ጋምቤላ የአኙአክ እና የኑር ጎሳዎች መኖሪያ ስትሆን የየራሳቸው ገበያ በጋምቤላ ውስጥ አላችው። ከተማዋ የአንድ ኤርፖርት ባለቤትና የጋምቤላ ብሄራዊ ፓርክ ተጓዳኝ ናት። ጋምቤላ የተመሰረተችብት ምክኒያት በባሮ ወንዝ ላይ ባላት አቀማመጥ ነው። ይህ ወንዝ በጊዜ ኢትዮጵያና እንግሊዝ ቡና ወዘተ. ወደ ሱዳንና ወደ ግብጽ ለመላክ ምቹ መንገድ መሆኑን ሁለቱም በማመናችው ነው። በ1902 እ.ኤ.አ. አጼ ምኒልክ ለእንግሊዝ ባሮ ወንዝ ላው አንድ ወደብ እንዲጠቀም ይፈቅዱና በ1907 እ.ኤ.አ. በስራ ላይ ከቀረጥ ቢሮ ጭምር ይውላል። በሱዳን የምድር ባቡር ኩባንያ የሚተዳደር የመርክብ አገልግሎት 1,366 ኪሎ ሜትር በመጓዝ ጋምቤላን ከካርቱም ጋር ያገናኛታል። በሪቻርድ ፓንክርስት ዝገባ መሰረት በክረምት በወር ሁለት ጊዜ መርከቦች ሲመላለሱ ወንዙን ሲወርዱ 7 ቀናት፣ ሲወጡ ደግሞ 11 ቀናት ይፈጅባቸው ነበር። ጋምቤላ በጣሊያን የምሰራቅ አፍሪካ ግዛት በ1936 እ.ኤ.አ. ተጠቃላ፥ በ1941 እ.ኤ.አ. በአንድ ከባድ ውጊያ በኋላ ወደ እንግሊዝ አስተዳደርነት ትዘዋውራ ነበር። ሱዳን ነጻ በወጣችበት በ1948 ዓ.ም. ለኢትዮጵያ ተመለሰች። በባሮ ላይ ያለው ወደብ በደርግ ጊዜ እንደተዘጋ ሆኖ፥ ይከፈት ይሆናል የሚል ተስፋ አለ። በሦስት ዞኖችና በአንድ ልዩ ወረዳ ሥር በሚገኙ 13 ወረዳዎች፣ በ241 ቀበሌዎችና በአንድ የከተማ አስተዳደር የተዋቀረችው ጋምቤላ ጠቅላላ የቆዳ ስፋቷ 30,065 ካሬ ኪሎ ሜትር ነው፡፡ ሃያ በመቶው የክልሉ መሬት በደን የተሸፈነ ነው፡፡ ጋምቤላ በሰሜንና በምሥራቅ ከኦሮሚያ ክልል ጋር ስትዋሰን፣ በደቡብ ምዕራብ ከአዲሲቱ ደቡብ ሱዳን ጋር በሰፊው ትዋሰናለች፡፡ ከአዲስ አበባ በ776 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው የጋምቤላ ከተማ በቅርቡ 100ኛ ዓመት የልደት በዓሏን ያከበረች ሲሆን፣ እንደ ብዙዎቹ የአገሪቱ ዕድሜ ጠገብ ከተሞች ዘርፈ ብዙ ችግሮችን የምትጋፈጥ የበረሃ ገነት ነች፡፡ ከ60 ሺሕ በላይ ነዋሪዎች ያላት ጋምቤላ በአብዛኛው የሚኖሩባት እንግሊዞች በቅኝ ግዛት ዘመን ሱዳንን በሚያስተዳድሩበት ወቅት ለወታደራዊም ሆነ ለንግድ እንቅስቃሴው መናኸሪያ በማድረግ ሲጠቀሙባት እንደነበር በታሪክ የሚነገርላት ጋምቤላ፣ ከ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ጀምሮ የኢትዮጵያ አካል እንደነበረችና በኋላም ሱዳን እ.ኤ.አ በ1956 ነፃነቷን ስትቀዳጅ በኢትዮጵያ የአስተዳደር ክልል ሙሉ ለሙሉ መካተቷም በታሪክ ድርሳናት ተወስቷል፡፡ በክልሉ አምስት ብሔረሰቦች ይኖራሉ፡፡ ጋምቤላ በእነዚህ ብሔረሰቦች የእርስ በርስ ግጭትና በአካባቢው ድንበርተኛ በሆነችው ሱዳን ለረዥም ዓመታት በቆየው የእርስ በርስ ጦርነት ስትታመስ መኖሯም ይታወቃል፡፡ ዚህም ከአገሪቱ ታላላቅ ተፋሰሶች አንዱ በሆነው የባሮ ወንዝ ላይ ረዥም የተባለውን ድልድይ በመገንባት የአካባቢውን ሁኔታ ሲያረጋጋ፣ ለፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያምም ለየት ያለ አድናቆትንና ፍቅርን ያስገኘላቸው አጋጣሚ እንደነበርም በአካባቢው ነዋሪዎች በስፋት ይወሳል፡፡ አሁንም ድረስ በከተማዋ ጋምቤላ አቋርጦ የሚያልፈው ባሮ ወንዝ ላይ በተገነባው ድልድይ በአንድ በኩል ብቻ በርከት ያለ ሕዝብ ሲጓጓዝ የተመለከተ ጎብኚ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ሲጠይቅ፣ ከነዋሪዎች ‹‹ኮሎኔሌ መንግሥቱ የተራመዱበት ጥግ ስለሆነ ነው›› የሚል ምላሽ ሊያገኝ ይችላል፡፡ በእርግጥ በተደጋጋሚ ጊዜ እንደሚደመጠው የቀድሞው መሪ በባሮ ወንዝ ላይ ባስገነቡት ድልድይ የአካባቢው ነዋሪዎች የእርስ በርስ ግንኙነታቸውን ከማጠናከር ባለፈ፣ በኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ተጠቃሚ በመሆናቸው እሳቸው ጥለው ያለፉት ከፍተኛ ቅርስ መሆኑን ይመሰክራሉ፡፡ በአንፃሩ የከተማው የትራፊክ አስተናባሪዎች እግረኞች ብቻ ሳይሆኑ ተሽከርካሪዎችም ጭምር በተራ የሚተላለፉት የድልድዩን ደኅንነት ለመጠበቅ ታስቦ እንደሆነ በመግለጽ የመጀመሪያውን አስተያየት ያጣጥሉታል፡፡ ‹‹መንግሥቱ የባሮን ድልድይ በማሠራቱ ዘለዓለማዊ ፍቅርን በእኛ ዘንድ አኑሯል፤›› ያሉት የዕድሜ ባለፀጋው አኩሉ ኦጆን፣ ምናልባትም ፕሬዚዳንቱ በቆዳ ቀለማቸው ለጋምቤላ ሕዝቦች ቅርብ ከመሆናቸው ጋር በተያያዘ ትክክለኛ የአገር መሪ እንደነበሩም በማወደስ ጭምር ፈገግታ የተሞላበት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ፡፡ የቀድሞው መሪ በጋምቤላ የባሮ ወንዝ ድልድይን ብቻ ሳይሆን የጋምቤላ አውሮፕላን ማረፊያን ያስገነቡ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ በአካባቢው ሕዝብ የተለየ ቦታ እንዳላቸው ቢነገርም፣ ጋምቤላ ከመጀመሪያው ጀምሮ በሕወሃት አስተዳደር ክፉኛ ተጎድታለች፤ በመሬቷ ልማትና በከርሰ ምድር ሃብቷ ምክንያት በዐባይ ጸሐዬና በዶ/ር ገብረአብ ባርናባስ የተመራ በ1994 የተጀመረው የዘር ማጥፋት አሁንም ሙሉ ለሙሉ ቆሟል ለማለት ያስቸግራል፣ በቅርቡ በመዥነገሮች ላይ የሕወሃት ወታደሮች የፈጸሙትን ጭፈጨፋ ስናስብ! በክልሏ የተፈጥሮ ሃብት ላይም የተካሄደውና የሚካሄደው ጭፍጨፋ በሃገራችን በሁሉም መልኩ በሲቪል ማኅበረስብና የመንግሥቱን መዋቅር በሚቆጣጠረው የንዑስ ብሄረሰብ ወኪል የሆነው በጦር ኃይል የሚደገፈው ሕወሃት የሚፈጽመው የጥፋትና የጠላትነንት ሥራ ብዙ ማስረጃዎች እየቀረቡበት ነው። የኢትዮጵያን ተተኪ የሌለው የተፈጥሮ ሃብት በብር 16.7 ሚሊዮን ክፍያ በባዕዳን በማስጨፍጨፍ፡ ሕወሃትና ጭፍሮቹን በሃገሪቱ ላይ ያላቸውን የጠላትነት ጥላቻ አረጋግጠዋል። ይህ ድርጊትም ባዕድ ቅኝ ገዥ ከሚያደርገው ተለይቶ የሚታይ አይደለም – በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ ጉማሬ ቀበሌ ውስጥ ይገኛል፡፡ የጉማሬ ደን ከ1,800 እስከ 2,200 ሜትር ከፍታ ላይ ደልዳላ ቦታ ይዞ ከተራራው ወደታች ሲወርድ ቁልቁለታማ ሸለቆዎች በብዛት ያሉበት ነው፡፡ ከዚህ ተራራማና በጥቅጥቅ ተፈጥሯዊ ደን የተሸፈነ ምድር በርካታ ወንዞችና ወንዞችን የሚፈጥሩ ምንጮች ይነሳሉ፡፡ በአጠቃላይ 40 የሚደርሱ ምንጮችና ወንዞች ከአባቢው የሚነሱ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ሻይ፣ ጋጃ፣ ካጃዲ፣ ፋኒና ቢታሽ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ከአካባቢው የሚነሱ የውኃ ምንጮች በኢትዮጵያ ከሚገኙ 12 ተፋሰሶች አንዱ የሆነው የባሮ አኮቦ ተፋሰስ አካል ናቸው፡፡ የጋምቤላ ክልል እስትንፋስ የሆነው ባሮ አኮቦ ወንዝ የነጭ ዓባይ ትልቅ ገባር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በሌላ በኩል ለውኃ አካላቱ መሠረት የሆነው የአካባቢ ተፈጥሯዊ ደን በርካታ አገር በቀል ዛፎችን ያካተተ ነው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ቀረሮና ገተማ ዛፎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የገተማ ዛፍ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴን ጨምሮ በርካታ ኢንቨስተሮችና የአካባቢው ንብ አናቢዎች ማር እንዲያመርቱ ምክንያት የሆነ ነው፡፡ የገተማ ዛፍ የተለየ ጥራት ያለው የማር ምርት ማስገኘት የሚችል መሆኑን የአካባቢው ማኅበረሰብ ይተርክለታል፡፡ ከማር ምርት በተጨማሪ ተፈጥሯዊው የጉማሬ ደን በርካታ ቅመማ ቅመሞች የሚገኝበት መሆኑም ይነገርለታል፡፡ ነገር ግን የህንዱ ኩባንያ ቬርዳንታ ሐርቨስትስ ያለ በቂ ጥናት ቦታውን መረከቡ የአካባቢውን ብዝኃ ሕይወት እየጎዳ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በ1997 ዓ.ም. ተመሥርቶ በ1999 ዓ.ም. ነው ሥራ የጀመረው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በቤንች ማጂ ዞን በ52 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ቴፒ ከተማ ውስጥ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ከተሞች
50491
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%A1%E1%8A%90%20%E1%8A%A5%E1%88%B5%E1%89%B5%E1%8A%95%E1%8D%8B%E1%88%B0%20%E1%8A%AD%E1%88%AD%E1%88%B5%E1%89%B6%E1%88%B5
አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ
አቡነ እስትንፋስ ክርስቶስ የስማቸው ትርጓሜ የክርስቶስ፣ የአብ ፣ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ማለት ነው ፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፊታቸው ላይ እፍ ብሎ ጸጋውን፣ በረከቱን ስላሳደረባቸው በዚህ ስም ይጠራሉ ፡፡ የጻድቁ፣ የአባታቸው ስም መልአከ ምክሩ ሲሆን ፤ የእናታቸው ወለተ ማርያም ይባላሉ ፡፡ የትውልድ ቦታቸው በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ዳውንት ዐወን ዓባይ የተባለ አካባቢ ነው ፡፡ የተፀነሱት ሚያዝያ ፰፤ የተወለዱት ደግሞ ታኅሣሥ ፰ ቀን ነው ፡፡ የሕይወት ታሪካቸው በተወለዱ ዕለት በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ ‹‹ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ›› በማለት እግዚአብሔርን አመሰግነዋል፡፡ የሕፃናትን አንደበት ለሚያናግሩ፣ ለሥላሴ እና ለእመቤታችን እንደዚሁም ለክርስቶስ መስቀል ዘጠኝ ጊዜ ሰግደዋል፡፡ በልጅነታቸው፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትገለጽላቸው ነበር፡፡ ያደጉትም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸው ነው፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት በደረሰ ጊዜም የመጻሕፍት ዂሉ ርእስ የሚኾን ፊደልንና የሐዋርያው ዮሐንስን መልእክት ደብረ ድባ በሚባል ቦታ ከመምህር ኪራኮስ ተምረዋል፡፡ የሐዋርያትን ሥራ፣ የቅዱስ ጳውሎስን መልእክት፣ የዳዊትን መዝሙር፣ እንደዚሁም ትርጓሜ መጻሕፍትን ተምረዋል፡፡ ከዚህ በኋላ በዘመኑ ከነበሩት ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የዲቁና መዓርግ ተቀበሉ፡፡ ከዚያም በሐይቅ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ገዳም መነኰሱ፡፡ ከዚያም ወደ ሕንጻ ደብረ ድባ ሔደው የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳሳት፣ የገዳማት አለቃ፣ የመነኮሳት አባት ከሚኾን ከአባ ሙሴ መዓርገ ቅስና፣ ቍምስና እና ኤጲስ ቆጶስነት በቅደም ተከተል ተቀብለዋል፡፡ ተጋድሎዋቸውና ታመራቸው አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ፣ ዐቢይ ጾምን ዐርባ ሌሊትና ዐርባ ቀን እኽልን ውኃ ሳይቀምሱ ይጾሙ ነበር፡፡ እግሮቻቸው እስኪያብጡ ድረስ ቆመው ይጸልዩ ነበር፡፡ ለሽፋሽፍቶቻቸውም ዕረፍትን አይሰጡአቸውም ነበር፡፡ በአንድ ወቅት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ገዳም ሲሔዱ ወደ ገዳሙ ለመግባት ሐይቁን የሚያሻግራቸው ቢያጡ ተንበርክከው ሲጸልዩ በቅዱስ ሚካኤል እጅ ደንገል (ታንኳ) ቀርቦላቸው ሐይቁን ተሻግረዋል፡፡ ዘጠኝ ዓመት ዓባይ ባሕር ውስጥ በራሳቸው ተዘቅዝቀው በመቆም ለኢትዮጵያ ሲጸልዩ ከቆዩ በኋላ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሳቸው መጥቶ ‹‹ከመነኮሳት ዂሉ ብልጫ ያለህ ወዳጄ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ፥ ኢትዮጵያን ምሬልሃለሁና ከዚህ ባሕር ውጣ›› ብሏቸዋል፡፡ ከዚያም ማረፊያቸው ወደ ኾነች ዳውንት (ደብረ አስጋጅ) በመመለስ ዐሥራ ሰባት ገዳማትን መሥርተዋል፡፡ ወደ ደብረ ዳሞ በሔዱ ጊዜም በትእምርተ መስቀል አማትበው ያለ ገመድ ከደብረ ዳሞ ተራራ ላይ በመውጣት ከአቡነ አረጋዊ ጋር (ከተሰወሩበት ቦት መጥተው) ተገናኝተዋል፡፡ በየገዳማቱ ሲዘዋወሩ ከሞላ ውኃ በደረሱ ጊዜ በመስቀል ምልክት አማትበው በእግራቸው እንደ ደረቅ መሬት እየረገጡ ይሻገሩ ነበር፡፡ አምስት አንበሶችና አምስት ነብሮች ይከተሏቸው ነበር፤ እነዚያም አንበሶችና ነብሮች የሚመገቡትን ባጡ ጊዜ ድንጋዩን ባርከው ሥጋ ያደረጉላቸው ነበር እነሱም ያንን ይመገቡ ነበር፡፡ የትግራይን አድባራትና ገዳማትን ለመጐብኘት ወደ ቅዱስ ያሬድ ደብር ሲደርሱ እመቤታችን ከቅዱስ ያሬድ (ከብሔረ ሕያዋን መጥቶ) እና ከልጅዋ ጋር ወደ እርሳቸው መጥታ ብዙ ተአምራትን አድርጋላቸዋለች፤ ከቅዱስ ያሬድም ተምረዋል፤ ቡራኬ ተቀብለዋል፡፡ የመጨረሻዎቻቸው ጊዜያት የጻድቁ የዕረፍታቸው ቀን በደረሰ ጊዜ እንደ ነጋሪት ቃልና እንደ ነጎድጓድ ያለ ድምፅ በሰማይ ተሰማ፤ እንደ ፀሐይ እና እንደ ጨረቃ እንደ ከዋክብት የሚያበሩ የተለያዩ መብራቶች ታዩ፡፡ መሬትም አራት ጊዜ ተንቀጠቀጠች፡፡ ተራሮችና ኮረብቶች እጅግ ተነዋወጡ፡፡ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በምትለይበት ሰዓት እንደ መብረቅ የሚጮኽ ታላቅ ድምፅ ከሰማይ ተሰማ፡፡ ያን ጊዜ ሰው ዂሉ፣ እንስሳት፣ አራዊት፣ ዛፎችና ቅጠሎች፣ ተራሮች፣ ኮረብቶች፣ ወፎችም በየወገናቸው አለቀሱ፡፡ ፀሐይና ጨረቃ ጨለሙ፤ ከዋክብትም ረገፉ፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በታላቅ ግርማ፣ በአንድነትና በሦስትነት እየተመሰገኑ መጡ፡፡ ኪሩቤል፣ ሱራፌል ከነማዕጥንታቸው፣ ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት፣ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት፣ ዐሥራ አምስቱ ነቢያት፣ ሰማዕታት ከቅዱስ እስጢፋኖስ እስከ ተፈጻሜተ ሰማዕት ሊቀ ጳጳስ ዼጥሮስ ድረስ ያሉት፣ ቅዱሳን መነኮሳት ከአባታቸው ከእንጦንስ ጋር መጡ ፡፡ የሰማዕታት እናታቸው፣ የመነኮሳትና የደናግል አክሊላቸው፣ ክብራቸው፣ መመኪያቸው፣ የሐዋርያት ስብከታቸው፣ የነቢያት ትንቢታቸው፣ የመላእክት እኅታቸው፣ የኃጥኣን ተስፋቸው፣ የፍጥረት ሁሉ አማላጃቸው፣ የምሕረት እናት፣ ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ደናግላንን አስከትላ መጣች፡፡ ጻድቁ አባታችን ከጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኋላ ለዚህ ክብር ያበቃቸውን እግዚአብሔርን አመስግነው በሰላም ዐረፉ፡፡ ዕረፍታቸውም ሚያዚያ ዘጠኝ ቀን ሲኾን፣ ያረፉበት ቦታም ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ዳውንት ከተማ ደብረ አስጋጅ ገዳም ነው፡፡ ከተቀበሉት ቃልኪዳን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ከጌታችን ከመድኀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከተቀበሉት ቃል ኪዳን ጥቂቱ ዝክራቸውን የዘከረ፣ መታሰቢያቸውን ያደረገ፣ ስማቸውን የጠራ፣ ገድላቸውን የጻፈ፣ ያጻፈ፣ ያነበበ፣ የተረጐመ፣ የሰማ፤ በፍጹም ልቡና ‹‹አምላከ እስትንፋሰ ክርስቶስ (የእስትንፋሰ ክርስቶስ አምላክ) ኀጢአቴን ይቅር በለኝ›› ብሎ የጸለየ ስሙ በሕይወት መጽሐፍ ይጻፍለታል፡፡ ለቤተ ክርስቲያናቸው መባዕ፣ ስንዴ፣ ዘይት፣ ዕጣን፣ ጧፍ የሰጠ ኀጢአቱ ይደመሰስለታል፤ በገነት፣ በመንግሥተ ሰማያት በደስታ ይኖራል፡፡ በስማቸው የተራቆተውን ያለበሰ፣ የተራበውን ያበላ፣ ያዘነውን ያረጋጋ፣ በመታሰበያቸው ዕለት ለአገልግሎት የሚፈለገውን መልካሙን ነገር ያደረገ ኀጢአቱ ይሰረይለታል፡፡ በየዓመቱ ሚያዚያ ፱ ቀን እና በየወሩ የዕረፍታቸውን መታሰቢያ በዓል ያከበረ፣ ዝክራቸውን የዘከረ ሰማያዊ ክብር ያገኛል፡፡ በስማቸው የጽዋ ማኅበር የሚጠጡ ሰዎች ቢኖሩ በመካከላቸው የጻድቁ አምላክ ይገኛል፡፡ ዝክራቸውን የዘከሩ፣ መታሰቢያቸውን ያደረጉ፣ በስማቸው የተማጸኑ፣ በገድላቸው የተሻሹ፣ በጠበላቸው የተጠመቁና የጠጡ መካኖች ልጅ ይወልዳሉ፡፡ ችግር ደርሶበት ስማቸውን የጠራ፣ ወንድ ወይም ሴት ልጁን በስማቸው የሰየመ፣ በበዓላቸው ቀን ቁራሽ እንጀራና ቀዝቃዛ ውኃ ለነዳያን የሰጠ ኀጢአቱ ይሰረይለታል ፡፡ ካደረጉአቸው ተአምራት መካከል ከፊሉ ከደቀ መዝሙራቸው ከልብሰ ክርስቶስ ጋር በጎዳና ሲሔዱ የደረቀ የሰው አጥንት አግኝተው ፈጽሞ ወደ እግዚአብሔር ሲለምኑ ያን ጊዜ በጸሎታቸው ኃይል ያ የሞተውና የደረቀው አጥንት ነፍስ ዘርቶ ተነሥቷል፡፡ የቀትር ጋኔን ለክፏት ልቧን ሰውሮአት የአገኘችውን ሰው እና እንስሳ በጥርሷ ትነክስ የነበረች አንዲት ሴት ሕመሟ ጸንቶባት ሞታ ሰዎች ሊቀብሯት ሲሉ የእስትንፋሰ ክርስቶስን መስቀልና መታጠቂያውን በአስከሬኑ ላይ ሲያስቀምጡት በእግዚአብሔር ኃይል ተነሥታለች፡፡ አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስ በብርሃን ሠረገላ ወደ ሰማይ ሲያርጉ ዓይኑ የጠፋ፣ እግሮቹ ልምሾ የኾኑ ሰው ዐይቷቸው ‹‹አባቴ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ፥ በጸሎትዎ ፈውሱኝ›› ብሎ ተማጸናቸው፡፡ አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስም ያንን ሰው አዝነውለት በእጃቸው ያለውን መሐረብ ወረወሩለት፡፡ በዚያን ጊዜ ልምሾ የነበሩ እግሮቹ ዳኑ፤ ዓይኑም በራለት፡፡ ስንዴ ዘርተው፣ ወይን፣ ጽድንም፣ ወይራን፣ ግራርንም ተክለው በአንዲት ቀን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ስንዴውን ለመሥዋዕት፣ ወይኑን ለቍርባን ዕለቱን በተአምራት አድርሰዋቸዋል ፡፡ ካረፉ በኋላ (በዐጸደ ነፍስ) ካደረጉአቸው ተአምራት መካከል ጥቂቶቹ በልጃቸው ዐይነ ሥውር መኾን ተጨንቀው የነበሩ አንዲት እናት እስትንፋሰ ክርስቶስ ልጃቸውን ቢፈውሱላቸው እንደሚመነኵሱ ስእለት ተስለው ጠበሉን ሲያስጠምቁት የልጃቸው ዐይኑ በራለት፡፡ ኾኖም ግን ተስለው የነበረውን ምንኵስና እንዳያደርጉ ዘመዶቻቸው ስለ ከለከሏቸው ልጃቸው ተመልሶ ዐይነ ሥውር ኾኗል፡፡ ወለተ ማርያም የተባሉ እናት ትዳር መሥርተው ለዐሥራ ሁለት ዓመታት ልጅ ሳይወልዱ ሲኖሩ የጻድቁን ገድል አዝለው በስማቸው ስም ቢማጸኑ ልጅ ለመውለድ በቅተዋል፡፡ ሊበተን የነበረውም ትዳራቸውም ተቃንቶላቸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር በጻድቁ አማላጅነት ከጡት ካንሰር በሽታ እንደ ተፈወሱ፣ ጤንነታቸው እንደ ተመለሰላቸው እኒህ እናት ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡ የጻድቁ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን በዓል ይዘክሩ የነበሩ ሰዎች ላም አካለ ጎደሎ ጥጃ ትወልዳለች፡፡ ከቤተሰቡ መካከል በእምነቷ ጠንካራ የነበረችው እኅታቸው ጥጃዋን በእስትንፋሰ ክርስቶስ ገድል ብታሻት በእግሯ ቆማ ሔዳለች፡፡ የእናቷንም ጡት ተንቀሳቅሳ ለመጥባት ችላለች፡፡ ለአምስት ዓመታት ሆዱ አብጦ የነበረ አንድ ዲያቆን የጻድቁ ገድል የተደገመበትን ጠበል ሲጠጣ ከሕመሙ ተፈውሷል፡፡ ወደ ደብሩ ለመሄድ በአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ስም እየተማጸኑ በገድላቸው በመጸለይና ሰውነታቸውን በማሻሸት፣ እንደዚሁም በገዳማቸው በሚገኘው በጠበላቸው በመጠመቅ፣ በእምነታቸው በመቀባት ብዙ ምእመናን አሁንም ከሕመማቸው እየተፈወሱ ናቸው፡፡ የጻድቁ ገዳም (ደብረ አስጋጅ) በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ዳውንት ከተማ አካባቢ ይገኛል፡፡ በረከት ለመቀበል ወደ ገዳሙ ለመሔድ ከወልድያ እስከ ዳውንት በመኪና የስምንት ሰዓታት መንገድ ይወስዳል፡፡ ከዳውንት ከተማ ወደ ገዳሙ አቅራቢያ የሚያደርሱ አነስተኛ ተሸከርካሪዎችም ይገኛሉ፡፡ ወደ ገዳሙ ለመግባት ለጠነከሩ የአንድ ሰዓት ያህል የእግር ጕዞ ይኖረዋል፡፡ የጻድቁ በዓለ ዕረፍት በሚከበርበት ዕለት (ሚያዝያ ዘጠኝ ቀን) ከወልድያ እስከ ገዳሙ የሚያደርሱ መጓጓዣዎች ስለሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያኑ ወደ ገዳሙ በመሔድ ከበረከቱ ተሳታፊ እንዲኾኑ ገዳሙ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ የጻድቁ ጸሎታቸው ፣ በረከታቸውና አማላጅነታቸው ከዂላችን ጋር ይኹን ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡ የበለጠ ለመረዳት እዚህ ላይ ይጫኑ
1549
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8D%E1%89%A5%E1%8D%85
ግብፅ
ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር (አረብኛ ) በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። ግብፅ የመጀመሪያ ቀደምት ስልጣኔ ያላት ሀገር ናት። ከ3000 ዓዓ የተነሳው ጥንታዊ የግብፅ ስልጣኔ፣ በስነ ቅርፅ፣ ኪነጥበብ፣ ምህንድስናና ቴክኖሎጂ የላቀ ሲሆን በቡዙ ስነ ቅሪትና ሳይንሳዊ ምርምር ላይ የዋለ ነው። በተጨማሪም ግብፅ ለሶስት ሺህ አመት በዘውዳዊ ግዛት ስትመራ ነበር። በ3150 ዓዓ ንጉስ ሜኔስ የግብፅ የተዋሀደ ስልጣኔ አስጀመረ። የታላቁ ጊዛው ፒራሚድ በ2600 ዓዓ በአራተኛው የግብዕ ስርወ መንግስት ፈርኦን በነበረው ኩፉ የተገነባ ሲሆን፣ በአለም አንደኛ የሆነ የቱሪስት መስህብነት ያለው ሀውልት ነው። ነገር ግን ይህ ፒራሚድ በወቅቱ የነበሩት የፈርኦኖች ሰይጣንን ማምለኪያ እና መናፍስት የመጥሪያም ሀውልት መሆኑም ይታውቃል። ይህ ሀውልት ለተጓዳኝ የሮማ ወይም የአሁኑ ምዕራብያውያን ስልጣኔ ተረፈ ምርት ሆኖ እያገለገለ ነው። በተጨማሪም የምዕራብያውያን አጋንንታዊ ማምለኪያ ምልክት ሊሆን ችሏል። ኢሉሚናቲ እና አሜሪካ በማህተሟ ላይ በመጠቀም የሚመጣውን ሰይጣናዊው አምባገነናዊው የአለም መንግስት የሚመኙበትን ዘዴ ያሳያል። ግብፅ በጥንት ዘመን የክርስትና ቁንጮ የሆነች ሀገር ነበረች፣ ነገር ግን በ7ተኛው ክፍለ ዘመን እስልምና ሲስፋፋ ወዲያውኑ የእስላም ሀገር ሆናለች። ግብፅ በ1922 ዓም ከእንግሊዝ ቀኝ ግዛት ስትወጣ፣ ከእስራኤል ጋር ብዙ የድንበር ጦርነት አድርጋልች። በ1978 ዓም፣ ግብፅ የጋዛን ግዛት በመተው እስራኤል እንደሀገር እንደሆነች ተገነዘበች። ከዛም በኋላም ግብፅ በብዙ የፓለቲካ አለመረጋጋት አሳልፋለች። ከ2011 ዓም አብዮት ጀምሮ ግብፅ በግማሽ የርዕሰ ብሄር አስተዳደር ትመራለች። የግብፅ ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ ኢል ሲዝ በብዙ ሀያሲያን አምባገነናዊ አመራር እንዳለው ተናግሯል። ግብፅ የክልል ሀያላን የሆነች ሀገር ናት። የግብፅ ህዝቦች ምንም እንኳን ፈሪሃ እግዚአብሄር ያደረባቸው ሀይማኖተኛ ቢሆኑም፣ ከምዕራብያውያን ጋር በመተባበር አዲሱን አምባገነናዊ የአለም መንግስት ለመመስረት እየነደፉበት ይገኛሉ። በተጨማሪም ግብፅ የሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አጠቃላይ ፓለቲካ ለመቆጣጠርና ሀያልነቷን ለማጠናከር ከአሜሪካ ጋር እየሰራችበት ይገኛል። ግብፅ በታሪክ ታዋቂ ጥንታዊ ሀይማኖት የነበራት ሲሆን ይህም ሀይማኖት ከጥንቆላና፣ መናፍስትን ከመሳብ ጋር ተያያዥነት አለው። ስለሆነም የግብፅ ሀይማኖት በምዕራብያውያን ዘንድ እጅግ ተወዳጅነት ያገኘ ሆኗል። ፍሪሜሰንሪ የተባለው ሰይጣናዊው ድርጅት የጥንታዊቷን ግብፅ ስልጣኔ በመጠቀም እንደራሱ ጥበብ በማዋል ታላቋን የሮማ (ምዕራብያውያን) ስልጣኔ አስነስቷል። ይህም ለሚያመጡት አምባገነናዊው የሰይጣን መንግስት ለመመስረት ሲባል ነው። ግብፅ የኒው ወርልድ ኦርደር፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአረብ ሊግ አባል ናት። ጥንታውያን የግብጽ ባለሥልጣኖች በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ከማየ አይኅ ቀጥሎ መጀመሪያ የአፍሪካ ሕዝብ የኖኅ ልጅ የካም ዘሮች ናቸው፤ ይህ አገር ሰናዖር ለሚሉት ቅርብ ስለ ነበር የባብል ግንብ ከተሠራ በኋላ ከዚህ ተነስተው ወደ ግብፅ ወረዱ። የግብጽ ቀድሞ ዘመን መንግሥት ዋና ጥንታዊ ነው፤ የመሠረተውም ፈርዖን ሜኒስ የተባለው ነው። ጸሓፊው ጊዮርጊስ ስንቄሎስ (፰፻ ዓ.ም. አካባቢ የጻፈው) ይህ ፈርዖን ሜኒስ በዕውነት የካም ልጅ ምጽራይም እንደ ነበረ ገመተ። ዳሩ ግን አባ አውሳብዮስ በጻፉት ዜና መዋዕል ዘንድ (፫፻፲፯ ዓ.ም. ተጽፎ)፣ የድሮ ግብጻዊው ባለታሪክ ማኔጦን (፫ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ.) ስለ ኋለኞቹ ግብጻውያን ሲጽፍ፣ ይኮሩበት የነበረው የታላቁ ጥንት ዘመን ከማየ አይህ አስቀድሞ እንዳለፈ፣ በኋላም በዚያው አገር ዳግመኛ ከሠፈረበት ከካም ልጅ ምጽራይም በውኑ እንደ ተወለዱ ጽፎ ነበር። ተመሳሳይ ታሪክ በእስላም ጸሐፊዎች በግብጻዊው እብን አብድ ኤል-ሀከም እና በፋርሳውያን አል-ታባሪና ሙሐመድ ቈንዳሚር መጻሕፍት ሲገኝ፣ ፒራሚዶች፣ እስፊንክስ ወዘተ. ሁሉ የተሠሩ ከጥፋት ውኃ በፊት በኖሩት ክፉ ዘሮች ሆኖ፣ ከዚያ በኋላ ግን አገሩ ለካም ተወላጅ ለምጽራይም ('ማሣር' ወይም 'መሥር') ተሠጠ ብለው ጻፉ። በግሪኩ ጸሐፊ ሄሮዶቶስ ዘንድ፣ የግብፅ ቀድሞ ዘመን የመጀመሪያው ፈርዖን ሜኒስ ነጭ አባይን ከመነሻው ወደ ጎን መለሰና ውሃው ይፈስበት በነበረው ላይ ሜምፊስ የተባለውን ከተማ ቆረቆረ። ታላቅ ንጉሥም ስለ ነበረ ከሞተ በኋላ ሕዝቡ እንደ አምላክ አድርገው አመለኩት። በዘመናዊ አስተሳስብ፣ ይህ ላይኛ ግብጽና ታችኛ ግብጽ ያዋሐደው መጀመርያው ፈርዖን መታወቂያ ለሥነ ቅርስ ከሚታወቀው ፈርዖን «ናርመር» ከተባለው ጋር አንድ ነው። ናርመር (ሜኒስ) አገሩን ካዋሐደ አስቀድሞ ሌሎችም ነገሥታት (ለምሳሌ ንጉሥ ጊንጥ) በአገሩ ክፍሎች ብቻ ላይ እንደ ነገሡ ከተገኙት ቅርሶች (የመንደሮቹ መኳያ ሰሌዳ ወይም የጊንጥ ዱላ እንደሚያሳይ) ይታወቃል። የሃይሮግሊፍ ቅርሶችና መዝገቦች ለማንበብ ችሎታው አሁን ስላለ፣ ሜኒስ ከነገሠ በኋላ የግብፅ ታሪክ በጥቂት መጠን ተገልጾአል። መጀመርያው ሥርወ መንግሥታት (፩ኛው እስከ ፮ኛው ድረስ) የቀድሞ ዘመን መንግሥት ይባላሉ። በ፩ኛው ሥርወ መንግሥት ሰባአዊ መስዋዕት በሰፊ ይደረግ ነበርና ከፈርዖኖቹ ጋራ ብዙ ሎሌዎች አብረው ይቀበሩ ነበር። የሔሩ ወገን በሴት ወገን ላይ ይበረታ ነበር። በ፪ኛው ሥርወ መንግሥት የፈርዖኖች መቃብር ከተማ ከላይኛ ግብጽ ወደ ታችኛ ግብጽ (ስሜኑ) ተዛወረ። በኋለኛ 2ኛው ሥርወ መንግሥት ዘመን የሴት ወገን ወኪል ፈርዖን ፐሪብሰን ተነሣና ያንጊዜ ትግሎች እንደ በዙ ይመስላል። በ፫ኛው ሥርወ መንግሥት መጀመርያ የሔሩ ወገን ለሥልጣን ተመልሶ፣ ነጨሪኸት የተባለው ፈርዖን የመጀመርያውን ሀረም (ፒራሚድ) አሠራ። ከርሱም በኋላ የተነሡት ታላላቅ ፈርዖኖች በጊዛ ሜዳ ላይ ፒራሚዶቻቸውን እንዲሁም የጊዛ ታላቅ እስፊንክስን ሠሩ። በ፬ኛውም ሥርወ መንግሥት የፈርዖኖች ዝሙት የገዛ እኅቶቻቸውን እስከሚያግቡ ድረስ ደረሰ። በ፭ኛው ሥርወ መንግሥት መጨረሻ ፈርዖኖች በሀረሞቻቸው ውስጥ የሀረም ጽሕፈቶች ያስቀረጹ ጀመር፤ እነኚህ ጽሕፈቶች የሔሩ ተከታዮች ወገን (ወይም «ደቂቃ ሔሩ») በሴት ተከታዮች ወገን ላይ የፈጸሙትን ጨካኝ የጭራቅነት ሥነ ስርዓት ይመሰክራሉ። ይህም አስጨናቂ ሁኔታ በ፮ኛው ሥርወ መንግሥት እየተቀጠለ ፈርዖኖቹ ዓለማቸውን ሁሉ ከነጎረቤቶቻቸውም ጋር በጽናት ይገዙ ነበር። ፮ኛው ሥርወ መንግሥት ከነገሠ በኋላ የግብፅ ታሪክ እጅግ ግልጽ ሆኖ አይታይም። በታሪክ ጸሐፍት እንደ ማኔጦን ዝርዝሮች በኩል፣ ለ፯ኛው-፰ኛው ሥርወ መንግሥታት በርካታ ስሞች ቢመዘገቡም፣ ከጥቂቶቹ ብቻ በስተቀር አንዳችም ሥነ ቅርሳዊ ማስረጃ ከቶ ስላልተገኘላቸው፣ ስሞች ብቻ ቀርተው በእውነት እንደ ኖሩ ወይም ዝም ብለው በማስመስል እንደ ተፈጠሩ አይታወቀም። ከቀድሞውም ዘመን በኋላ በእርግጥኛነት የነገሡት መጀመርያ ፈርዖኖች የግብጽ መካከለኛውን ዘመን መንግሥት የመሠረቱት በስማቸውም ውስጥ «ታ-ዊ» (ሁለቱ አገራት ወይም በዕብራይስጥ ምስራይም) የተባሉት ናቸው። የግሪክ ጸሐፍት አፈ ታሪክ በ6ኛው ሥርወ መንግሥት መጨረሻ ኒቶክሪስ የተባለች ሴት የአገሩ ንግሥት እንደ ሆነች የሄሮዶቶስና የማኔጦን ታሪኮች ይነግራሉ። ሄሮዶቶስ እንደሚለው፣ ወንድሙዋን ግብፆች ስለ ገደሉባት እሷም ልትበቀልለት አሰበች። ለዚሁ ጉዳይ ከመሬት ውስጥ አንድ ታላቅ አዳራሽ አሠራች። ከዚያም ታላቅ ግብር አዘጋጅታ የወንድሙዋን ገዳዮች ወደዚሁ ግብር ጠራቻቸው። የተጠሩትም በግብፅ ግዛት የታወቁ ክቡራን ነበሩ። እንዲሁ ሆኖ ሳለ በድንገት ከውጪ በራሳቸው ላይ ውካታና ፍጅት ጩኸትም ተነሳ። የጥፋት ውሃ አዳራሹን ሰብሮ ገባ። ንግሥት ኒቶክሪስ አስቀድማ የወንዙን ውሃ በሚስጥር ወደ አዳራሹ እንዲገባ አድርጋ ነበርና ውሃው በዚያ ታላቅ ግብር ላይ እንዲለቀቅ አደረገች። በዚያም የገቡ ሁሉ ሰጥመው ቀሩ። ይህ የኒቶክሪስ ታሪክ በሄሮዶቶስም ሆነ በማኔጦን ቢገኝም፣ በዘመናዊ ሥነ ቅርስ አስተያየት ለዘመንዋ ምንም ማስረጃ ስላልተገኘ አሁን እንደ አፈ ታሪካዊ ንግሥት ብቻ ትቆጠራለች። በግሪኮች የታሪክ ጸሐፍት ዘንድ ሌላ ስመ ጥሩ ፈርዖን ሲሶስትሪስ ነበር። ይህ ንጉሥ ዓለምን ለማሸነፍ አስቦ ከግብፅ ሲነሣ የሚሊዮን እኩሌታ የሚሆኑ እግረኛ ወታደሮች፣ ፳፬ ሺህ ፈረሰኞች፤ ፳፯ ሺህ የተሰናዱ ሠረገሎች እንደ ነበሩት ይተረኩ ነበር። ዝና ፈላጊነቱ በክብር ተፈጸመለትና ትልቅ ድል አገኘ። በየሄደበት ስፍራ ሁሉ ከእብነ በረድ የተሠራ ሐውልት አቆመ። የሚመጣው ትውልድ እንዳይረሳው ባቆመው ሐውልት ላይ ጽሕፈት እንዲቀረጽበት አደረገ። በብዝዎቹ ሐውልት ላይ እንዲህ የሚል ቃል ተጽፎአል። «ንጉሠ ነገሥት ሲሶስትሪስ በጦር ሠራዊቱ ኅይሉ ይህን አገር አሸንፎዋል» ነገር ግን ዘመናዊ የታሪክ ጸሓፊዎች እንደዚህ አላደረገም ብለው ይጠራጠራሉ። በማኔጦን ነገሥታት ዝርዝር «ሴሶስትሪስ» የሚባል ፈርዖን በ12ኛው ሥርወ መንግሥት በፈርዖን 3 ሰኑስረት (ሰንዎስረት) ፋንታ ይታያል። ስለዚህ የሴሶስትሪስ አፈ ታሪክ ከሰንዎስረት ትዝታ እንደ ተወረደ ይታመናል። ጵቶልሚዮስና ንግሥት ክሌዎፓትራ ሺሻክ የተባለ የግብፅ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን ስለ ያዛት የሰሎሞን ቤተ መቅደስ በዝብዞ ንዋየ ቅድሳቱን ሁሉ ጠርጉ ወሰደው። አሚኖፌስ የተባለ ስመ ጥሩ የግብፅ ንጉሥ ነበር፤ ይህም ምናልባት ለስሙ መጥሪያ (ለመታሰቢያው) ብሎ አንድ ትልቅ መቅደስና ምስል ያቆመ ሜምኖን የተባለው ንጉሥ ሳይሆን አይቀርም። የዚህም ፍራሽ እስከ ዛሬ በቴቤስ ይታያል። ያቆመውም የድንጋይ ምስል ፀሓይ ስትወጣ ደስ የሚያሰኝ ቃል ፀሓይ ስትጠልቅ የኅዘን ቃል ያሰማል ይባላል። ዛሬም በዚያ የሚያልፉ መንገደኞች ድምፁን የሚሰሙ ይመስላቸዋል። ፭፻፳፭ ዓመት ከዘመነ ክርስትና በፊት ካምቢሲስ ንጉሠ ፋርስ ግብፅን ድል አድርጎ ነበረና ሳሜኒቱስ የተባለውን የግብፅን ንጉሥ የወይፈን ደም በግድ ስለ አስጠጣው እንደ መርዝ ሆነበትና በዚሁ ጠንቅ ሞተ። ፫፻፴፪ ዓመት ከዘመነ ክርስትና በፊት የመቄዶንያው ንጉሥ ታላቁ እስክንድር ግብፅን ድል አድርጎት ነበር። በዚህ ስፍራ እስክንድሪያ የተባለ አንድ ስመ ጥሩ ከተማ ሠራ። ይህም ከተማ በዓለም ከታወቁት ከተሞች እጅግ ጥሩ ሆኖ የተሠራና መሰል የሌለው አያል መቶ ዓመት የቆየ ቤተ መንግሥት መሆኑ ታውቆዋል። የጥንቱ ሥራው ፈራርሶ ዛሬ የሚታየው እስክንድሪያ ከጥንቱ በጣም ያነሰ ነው። እስክንድር ሲሞት በዚሁ በእስክንድርያ ተቀበረ። ይኸው ከተማ ስመ ጥሩ በመሆኑ እስከ ዛሬ በግብፅ ዋና የንግድ ሁለተኛ ከተማ ተብሎ ይጠራል። እስክንድር የሱ ጀኔራል የነበረውን ጵቶልሚዎስን አገሩን እንዲገዛ ሾመው። ከጵቶልሚዎስ ጀምሮ ተወላጆቹ ሁሉ የንጉሥ ዘር ተብለው ሁሉም ጵቶልሚዎስ ተብለዋል። ፪፻፺፬ ዓመት ገዝተዋል። ከነዚህም በመጨረሻ የነገሠው ጵቶልሚዎስ ዲዮናስዮስ ይባላል። በላዮ የገዛ ሚስቱ ተነሥታ ሸፈተችበትና ተዋጋችው። ጵቶልሚዎስ ዲዮናስዮስ በመጨረሻ ድል ሆነና ለማምለጥ የማይሆንበት ቢሆን በነጭ ዐባይ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ሰጠመ። ሚስቱ ክሌዎፓትራ የተባለች የግብፅ ዋና ገዢ ሆነች። አሉ ተብለው ከሚጠሩት ቆነጃጅት አንዲቱ እርስዋ ነበረች። ስጦታዋና ተፈጥሮዋ ከውበትዋ ጋር የተካከሉ ነበሩ። ዳሩ ግን ክፉ ነበረች። ከሠራችው ሁሉ እጅግ የሚያሰቅቀው ነገር ያሥራ አንድ ዓመት ሕፃን የነበረውን የገዛ ወንድምዋን በመርዝ ማስገደልዋ ነው። ምንም ክፋትዋን ዓለም ቢያውቀው እኔ ነኝ ያለ ጀግና የውበት ማጥመጃዋን ሊቃወም የሚችል አልተገኘም። ማርክ አንቶኒ የተባለ የሮማ ጀኔራል በግሪክ አገር ፊሊጵ በተባለች አውራጃ ብሩተስንና ካሲውስን ድል ባደረገ ጊዜ ከሜዴቴራኒያን ባሕር በሰሜን ምሥራቅ ወደምትሆን ወደ ሲሲሊያ እንድትመጣ ክሌዎፓትራን አስጠራት። ምክንያቱም ለብሩተስ ረድታ ነበርና ሊቀጣት አስቦ ነበር። ክሌዎፓትራ ጥሪው እንደ ደረሳት እሺ ብላ በፍጥነት ተነሥታ በተለይ በወርቅ ባጌጠ ታንኳ ገባች። ታንኳው በሽራው ፈንታ ዋጋው የበዛ የከበረ ሐር ነበረው። ታንኳውን በብር መቅዘፊያ የሚቀዝፉት የተወደዱ ቆነጃጅት ነበሩ። ንግሥት ክሌዎፓትራ ሐር ተጋርዶላት በመርከቡ ተደግፋ ተቀምጣ ነበረች። እንደዚህ ሁና ሲድኑስ በተባለው ወንዝ ተንሳፈፈች። ያለችበትም ታንኳ እጅግ ያማረ ነበር። እርስዋም ራስዋ የተወደደች ነበረች። የሚታየው ሁለመናዋ ሕልም ይመስል ነበር። ከታንኳው መጋረጃ ነፋስ እየጠቀሰ የሚወስደው ሽቶ እያወደ ክሌዎፓትራ እንደ ተቃረበች ማርክ አንቶኒን አስጠነቀቀው። ከሩቅ ልብ የሚነካ የሙዚቃ ድምፅ ይሰማ ነበር። ቀጥሎ የብር መቅዘፊያው ሲብለጨለጭ ከሩቅ ይታይ ነበር። ነገር ግን አንቶኒ የግብፆችን ንግሥት በተመለከተ ጊዜ ምንም አላሰበም። ማርክ አንቶኒ ከክሌዎፓትራ እስኪገናኝ ድረስ ክቡር ሰውና ጀግና መሆኑን አሳየ እንጂ ከዚያ በኋላ ግን ፍጹም እንደ ባሪያዋ ሆነ። ከክሌዎፓትራና ከርሱ ክፉ አካሄድ የተነሣ ኦክታቢዎስ ከተባለ ከሌላ የሮማ ጀኔራል ጋር በግሪክ አገር አክቲውም በተባለች አውራጃ ላይ ተዋግተው አንቶኒ ድል ሆነና በገዛ ሰይፉ ወድቆ ሞተ። ክሌዎፓትራም ኦክታቢዎስ በሕይወትዋ ወደ ሮማ የወሰዳት እንደ ሆነ በሕዝብ መኻከል እንደሚያጋልጣት ተረዳችው። ስለዚህ ለመታገሥ የማይችል ሲሆንባት ጊዜ በግብፅ አገር አንድ ዐይነት በተናከሰ ጊዜ ሕመሙ የማይሰማ መርዛም እባብ ስላለ ክሌዎፓትራ ከንደዚህ ያለ መርዛም እባብ አንዱን አሲዛ አስመጥታ ሰውነቷን አስነከሰች። ትንሽ ቆይታ ሁለመናዋ ደነዘዘ አበጠ ወዲያው ልቡዋ መምታቱን አቆመ። ውበት የነበራት ክፋዩቱ የግብፅ ንግሥት ክሌዎፓትራ እንደዚህ ሆና ፴ ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት ሞተች። ተከታይ ታሪክ ከንግሥት ክሌዎፓትራ ሞት በኋላ ግብፅ ለሮማ መንግሥት ተገዛና እስከ ዘመነ ክርስትና ፮፻፵ ዓመት ድረስ የምሥራቅ መንግሥት እየተባለ ለሮማ እንደ ተገዛ ቆየ። ከዚህ በኋላ ሳራሲኖች ድል አደረጉትና እስከ ፮፻ ዓመት ቆየ። የሳራሲን ገዦች ያሠለጠኗቸው ማምሉኮች የተባሉት የገዛ ዘበኞቻቸው ሳራሲኖችን ከዙፋናቸው ዘርጥጠው አወረዷቸው። ቱርክ መጥቶ ድል እስኪያደርጋቸው ድረስ ማምሉኮች ግብፅን እስከ ፲፯፻፱ ገዝተዋል። ቱርኮችም ግብፅን እስከ ፲፯፻፺፰ ዓመት ገዝተዋል። ከዚህ በኋላ ናፖሊዮን ቦናፓርቲ አርባ ሺህ የሚሆን የጦር ሠራዊት ከፈረንሳይ አገር አምጥቶ፤ ግብፅን ወረረ። ቱርኮችም ግብፅን ከያዙ ወዲህ ማምሉክ የተባለውን ጭፍራ ወደ ሥራቸው አግብተው ጠብቀውት ነበርና እነዚህ ተስፋ እስኪቆርጡ ድረስ ተከላከሉ። ጦርነቱን የሚዋጉበት ስፍራ በፒራሚዱ አጠገብ ነበር። በዚያ ሲዋጉ ሳሉ እኩሌቶቹ እዚያው ታረዱ። ሌሎቹም እየዘለሉ ወደ ነጭ ዐባይ ወንዝ ባሕር ሰጠሙ። ከዚህ ጦርነነት በኋላ ናፖሊዮን ቶሎ ብሎ ወዲያው ወደ ፈረንሳይ አገር ተመለሰ እንጂ በዚህ አልዘገየም። ሲሄድም ጀኔራል ክሌበር የተባለውን ለፈረንሳይ ጦር ጠቅላይ አድርጎት ሄደ። ጀኔራል ክሌበር ጀግና ሰው ነበር። ዳሩ ግን ጨካኝ ነበርና ጨካኝነቱ ሕይወቱን እስከ ማጣት አደረሰው። ይኸው ጨካኙ ጀኔራል አንድ ቀን ሼህ ሳዳ የሚባል አንድ ሽማግሌ እስላም አገኘና ውስጥ እግሩን በከዘራ አስደበደበው። ወዲያው ትንሽ እንደ ቆየ ጀኔራሉ ወደ መስጊድ ገብቶ ሳለ አንድ የተናደደ እስላም ገሠገሠና በጩቤ ቢሽጥበት ያን ጊዜውኑ ሞተ። በ፲፰፻፩ ዓመት እንግሊዝ ፈርንሳዮችን ከግብፅ ለማስወጣት ከብዙ ጦር ጋራ ሰር ራልፍ አቤሮክሮምቢን ሰደደው። ጀኔራል መኑ የፈረንሳይ ኮማንደር ነበር። አቡኬር ላይ ተዋጉና ሰር ራልፍ አቤሮክሮምቢ ድል አደረገው። ዳሩ ግን እርሱም ራሱ ክፉኛ ቆስሎ ነበር። በዚያው ዓመት የፈርንሳይ ጦር ተሸነፈና ከግብፅ ወጥቶ በመርከብ ተሳፍሮ ወደ ፈረንሳይ አገር ተመለሰ። ዳሩ ግን ባላገሮቹ ከፊተኞቹ ገዢዎቻቸው ከቱርኮች ይልቅ የፈረንሳይ ጀኔራል ቅን ፍርድ እየፈረደ በመልካም አገዛዝ በደንብና በሕግ ይገዛቸው ነበርና በመሄዱ እጅግ አዝነው ተላቀሱ። የዛሬው የግብፅ ዋና ከተማ ትልቁ ካይሮ ነው። ቀድሞ ከነበረው ይልቅ የዛሬው በጣም ትንሽ ነው። ነገር ግን ፫፻ ሺህ ሰዎች ይኖሩበታል። የቤት ሥራ አሠራር ዕውቀትና የድንጋይ መውቀር ብልሀት ከሦስትና ከአራት ሺሕ ዓመት በፊት ብዙ ሚሊዮን ሕዝብ እንደ ነበረ እጅግ ለዐይን ያማሩ ታላላቅና ሰፋፊ የነበሩ የከተሞቻቸው ፍራሽ በመገኘታቸው እንረዳለን። በጥንቱም ሆነ ወይም በዛሬው አስተያየት ስንገምተው እጅግ ደምቆ የሚታይ ከተማ እንደ ቴቤስ ያለ አይገኝም። ባለመቶ በር ከተማ ይሉታል። በጦር ጊዜ ከዚህ ከተማ በያንዳንዱ በር የሚወጣው የጦር ሠራዊት እንደሚከተለው ነው። መሣሪያቸው የተሰናዳ ፪፻ ሠረገሎችና ፪ ሺሕ ወታደሮች ናቸው። ከ፳፬፻ ዓመት በፊት የነበረ ካምቢሲስ የተባለ የፋርስ ንጉሥ በነበረበት ዘመን ቴቤስ ፈርሶ ነበር። የከተማው ፍራሽ ከነጭ ዐባይ ወንዝ ግራና ቀኝ ፳፯ ማይል ርቀት ተበታትኖ እስከ ዛሬ ይታያል። ከሐውልቱም ያያሎቹ ውፍረት ፲፪ ጫማ (ፊት) ይሆናል። ከግብፆች ነገሥታት አንደኛው ዙሪያው አርባ አምስት ማይል የሚሆን ትልቅ ጉድጓድ ቆፍራችሁ ወደታች ጥልቅነት ያለው ባሕር ይሁን ብሎ ሕዝቡን አዘዛቸው። አንደኛው ንጉሥ ደግሞ ከመሬት ውስጥ አስቆፍሮ ከዕብነ በረድ የታነጸ ሦስት ሺሕ ጓዳ ያለው አዳራሽ አሠራ። ለዚህም ዘወርዋራ መንገድ ነበረው። ከፍ ባለው ጓዳ አንዲት የተቀደሰች አዞና ግብፆችም የሚያመልኩዋቸው ሌሎች አራዊት ነበሩ። ከምድር በታች ባለው ጓዳ የግብፃውያን ነገሥታት ዐፅም ተጋድሞአል። ደግሞ አንደ የሚያስደንቀው ሥራ መሬቱን ወደ ውስጥ ቆፍረው አለቱ ሲወጣ ያንን ወቅረው የድንጋይ ምሰሶ ያደርጉታል። ውስጥ ለውስጥ ጋሌሪ የደርብ መንገድ እያደረጉ ይሠሩታል። በዚህ ውስጥ ከሺሕ ዓመት በፊት የሞተውን ሰው ሬሳ አጋድመውት ይገኛል። ሳይለወጥ ልክ እንደ ተቀበረ ጊዜ ሆኖ ይታያል። ይህንንም ሙሚስ ይሉታል። የግብፅ ፒራሚድ በነጭ ዐባይ ወንዝ ዳር ይገኛል። ታላቁ ፒራሚድ ከፍታው ፭፻ ጫማ (ፊት) ነው። የግብፅ ፒራሚዶች የተሠሩበትን ዘመን የሠራቸውንም ሰው ማን እንደሆነ ከቶ አይታወቅም። ለመሆኑ ግን ለመቃብራቸውና ለዘለዓለም መታሰቢያ እንዲሆኑዋቸው ጥንታውያን የግብፅ ነገሥታት አሠርተቀቸዋል ይባላል። ነገር ግን ፒራሚዱ ሳይፈርስና ሳይናድ ምንም ብዙ ዘመን ቢቆይ የሠሩት ነገሥታት እነማን እንደ ሆኑ ስማቸው ተረስቷል። በቴቤስ አጠገብ ባንድ ሜዳ ላይ ወንድና ሴት ሆነው የሰው መልክ የሚመስሉ ሁሉ ታላላቅ ሐውልቶች አሉ፤ ቁመታቸውም ፶ ጫማ (ፊት) ይሆናል። በግብፆች መኻከል ከሚገኘው ከቀድሞ ሥራ ሁሉ በጣም የሚያስደንቅ ሲፊክስ የሚሉት ነገር ነው። ይኸውም ከታች አካሉ የአንበሳ ሆኖ ከላይ ከራሱ ትልቅ የሴት መልክ ነው። ዛሬ እንደሚታየው ከታች ያለው አካሉ በአሸዋ ውስጥ ተቀብሯል። የላይኛው ክፍል ከምድር በላይ የሚታየው ራሱና አንገቱ ነው። ይኸውም ቁመቱ ፸ ጫማ (ፊት) ነው። የተጠረበው ከአለት ድንጋይ ነው። በሩቁ ለተመለከተው ሰው አፍንጫዋ ደፍጣጣ የሆነች ሴት ከአሸዋ ውስጥ ብቅ ያለች ይመስላል። በጥንት ቴቤስ አጠገብ ያለው ሉክሶር የተባለው ከተማ ፍራሽ ለተመልካቹ የሚያስደንቅ ሁኖ ያለመጠን ትልቅ ነው። ከመቅደሶቹ አንዱ የጥንት ሥራ ስመ ጥሩ ይመስላል። ግብፃውያን ይህን የሚያስደንቅ ሥራ ሲሠሩበት በነበሩ ዘመን ከዛሬ ይልቅ የዚያን ጊዜ ብዙ ጥበብ ዐዋቂዎችና የተማሩ ሰዎች እንደነበሩ ይታያል። ጥበባቸውንና ዕውቀታቸው ከፍ ያለ እንደ ነበረ ተመልክተው የሌሎች አገር ሰዎች እንደ አስማተኞች ይገምቱዋቸው ነበር። ግብፆች ልማደ አገር ከንቱ አምልኮት ነበራቸው። ዋናዩቱም ጣዖታቸው ኢሲስ ትባላለች፤ ባልዋም ኦሲሪስ ይባላል። ምስላቸውን ሠርተው ለነዚህ ይሰግዱላቸዋል። ኢሲስ በጣም የተከበረች ጣዖት ናት፤ ሕዝቡም አያሎች መቅደሶች ሠርተውላታል፤ በዚህም ያመልኩዋታል። ስሜን አፍሪቃ
9300
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9A%E1%8A%AB%E1%8A%A4%E1%88%8D
ሚካኤል
ሚካኤል (በዕብራይስጥ: ‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል, ሲተረጎም፡ 'ማንነው እንደ እግዚአብሔር?'; በግሪክ: , ሲነበብ፡ ; በላቲን: -ሲነበብ፡ ሚካኤል; በአረቢኛ: ‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል) በክርስትና በአይሁድ በእስልምና እንዲሁም በመላዕክት አማላጅነት በሚያምኑ ሃይማኖቶች የመላዕክት ሁሉ አለቃ ሊቀ መላዕክት ተብሎ ይጠራል መላእክት ቁጥራቸው እጅግ ብዙ ቢሆንም በ ፺፱ኙ ነገደ መላእክት የተከፈሉና አለቆችም ያሏቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ሁሉ መላእክት አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ በትህትናው ልዕልናን ያገኘው ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠው ክብር ከማንኛውም መልአክ የበለጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡ የቅዱስ ማካኤልን ድርሳን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ ድርሳነ ሚካኤል በተጨማሪም ስለ መላእክት ከመጽሐፍ ቅዱስ ለመረዳት እነዚህን ጥቅሶች ይመለከቱ ሰውን ይረዳሉ ዘፍ.16፡7/ ዘፍ.18፡15/ ዘጸ.23፡20/ መሳ6፡11/ 1ኛነገ.19፡5/ 2ኛነገ 6፡15/ ዳን.8፡15-19/ ዳን.3፡17/ ት.ዘካ.1፡12/ ማቴ.18፡10/ሉቃ. 1፡26/ ሉቃ.13፡6/ ዩሐ.20፡11/ ሐዋ.12፡6/ ራዕይ 12፡7/ ስግደት ይገባቸዋል ዘፍ.19፡1-2/ ዘኁ.22፡31/ ኢያሱ 5፡12/ መሳ.13፡2/ 1ኛ ዜና 21፡1-7/ ዳን.8፡15 የቅዱስ ሚካኤል ስሞች ሚካኤል ማለት << መኑ ከመ አምላክ (እግዚአብሔር) እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው>> ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ ንጹሕ ርህሩህ ኃይል ረቂቅ ማነው መልሱ የለም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ፣…ናቸው፡፡ መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ - ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡ መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡ መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል ለማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ሁሉ ልዕልና ላይ ትሕትናን ደርቦ የያዘ በጸሎቱ ተማጽኖ በተራዳኢነት አምኖ ለሚለምነው ሁሉ ፈጥኖ በመድረስ ከሠራዊተ አጋንንት ተንኰል የሚያድን መልአክ ነው፡፡ ወደ ቅዱስ መጽሐፍ ስንገባ ለቅዱስ ሚካኤል የተሰጠውን ክብርና ባለሟልነት እንዲሁም የሠራቸውን ሥራዎች እንመለከታለን፡፡ በመጀመሪያ (ኢያሱ 5÷13-15) እንዲህ ይላል፡፡ ‹‹እንዲህም ሆነ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ዓይኑን አንሥቶ ተመለከተ፡፡ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ ነበር፡፡ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን አለው፡፡ እርሱም አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ አለ፡፡ ኢያሱም ወደ ምድር በግምባሩ ተደፍቶ ሰገደ፡፡ ጌታዬ ለባሪያው የሚነግረው ምንድን ነው አለው፡፡ የእግዚአብሔርም ሠራዊት አለቃ ኢያሱን አንተ የቆምህበት ሥፍራ የተቀደሰ ነውና ጫማህን በፊቱ አውልቅ አለው፡፡ ኢያሱም እንዲሁ አደረገ ይላል፡፡ ይህን ጥቅስ ልብ ብለን ብናጤነው ለሌላው ሁሉ መርህ ይሆናልና ጥቂት ለማብራራት እንሞክራለን፡፡ እንዲሁም እግዚአብሔር ራሱ ለኢያሱ ‹‹…በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም ከሙሴ ጋር እንደሆነው እንዲሁ ካንተ ጋር እሆናለሁ አልጥልህም አልተውህም፡፡…›› (ኢያሱ 1÷1-9) በማለት ምን ያህል እንዳከበረው ያስረዳል፡፡ እስራኤላውያን አሞራውያንን በወጉ ጊዜ ቀኑ ስለመሸባቸው ከመደበኛው የተፈጥሮ ሕግ ውጭ ቀኑ እንደማይጨልምና መዓልቱ እንዲረዝም ኢያሱ በጸሎት ፈጣሪውን ስለጠየቀ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ቀኑን አስረዝሞ ከሰማይ በረድ አዝንሞ ጠላቶቻቸውን በማጥፋት የፈጸመውን አስደናቂ ተአምር እንዲህ ብሎ ጸፏል፡፡ ‹‹...ፀሐይም በሰማይ መካከል ዘገየ አንድ ቀንም ሙሉ ያህል ለመግባት አልቸኰለም፤ እግዚአብሔር ለእስራኤል ይዋጋ ነበርና እግዚአብሔር የሰውን ቃል (ልመና) የሰማበት እንደዚያ ያለ ቀን ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ አልነበረም›› (ኢያ 10÷12-14) በማለት ተገልጿል፡፡ በጠቅላላው ከኢያሪኮ ጀምሮ ታላላቅ የአሕዛብ ምሽጐችን አፍርሶ አሕዛብን አጥፍቶ እግዚአብሔር ለአብርሃም ለይስሐቅ ለያዕቆብ የማለላቸውን የተስፋይቱን ምድር ለልጆቻቸው ያወረሰ ኢያሱ ነው፡፡ ይህ የእስራኤል መሪ በእጅ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ የተገለጸለት ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን አላወቀም፡፡ ከቃሉ እንደምንረዳው ከራሱ ወገን ወይም ከጠላቶቹ ወገን የሆነ አንድ ወታደር መስሎት ነበር፡፡ መልአኩ በሰው አምሳል ስለተገለጸለት አላወቀውም ነበር፡፡ ያነጋገረውም ያለ ፍርሃት ያለ ጭንቀት ያለድንጋጤ ወታደሮቹን እንደሚያነጋግር ዘና ብሎ ነው፡፡ ሆኖም ከመልአኩ የተሰጠው መልስ ታላቅ መሪና ነቢይ የሆነውን የኢያሱን አስተሳሰብ ለወጠው፡፡ ይኸውም <<ከወገኖችህ ወይም ከጠላቶችህ አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ>> የሚለውን ቃል ሲሰማ ኢያሱ በፊቱ የቆመው ተራ ወታደር ሳይሆን የመላእክት ሠራዊት አለቃ ከሙሴ ሳይለይ የእስራኤልን ሕዝብ የሚጠብቅ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን ሲረዳ ለመልአኩ ክብር መስጠት ስለሚገባ የአክብሮት ስግደት ሰገደለት፤ <<ጌታዬ ለባሪያው የሚነግረው ምንድነው>> በማለት በትህትና ጠየቀ፡፡ ጌታዬ አንተ ቅዱስ ሚካኤል ለኔ ለባሪያህ ለኢያሱ የምትነግረኝ ምንድነው; በማለቱ የእግዚአብሔርን ክብር ለፍጡር መስጠቱ አይደለም መላእክት ጌቶች ይባላሉ፡፡ ጌትነታቸውም የጸጋ ጌትነት ነው፡፡ ኢያሱ መልአኩን ጌታዬ ብሎ ከጠራው እኛማ ኃጢአተኞች ጌታዬ፤ ቀዱስ ሚካኤል ለኔ ለባሪያህ ጸልይልኝ መጥተህ አድነኝ…በማለት የአክብሮት (የጸጋ) ስግደት በመስገድ ብንለምነው ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ውጭ አልወጣንም፡፡ የፈጣሪን ክብር ለፍጡር አልሰጠንም፡፡ ተሳስታችኋል የሚለን ሰው ቢኖር እኛ አብነት ያደረግነው የእግዚአብሔር ወዳጅ ኢያሱን ስለሆነ ኢያሱም ተሳስተሃል ይባል፡፡ መልአኩም ኢያሱ ያቀረበለትን የአክብሮት ስግደትና ጥያቄ በመቀበል ከእግዚአብሔር የተሰጠውን መልእክት ነገረው፡፡ ኢያሱም ትእዛዙን ፈጸመ፡፡ የእግዚአብሔር ሠራዊት ጌታ ይህም ማለት መላእክትን ፈጥሮ የሚገዛ፣ የሚያዛቸው፣ የሚቀድሳቸው ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ የሚለው ከፈጣሪ በታች በመላእክት ላይ በፈጣሪ የተሾመ ማለት ነው፡፡ መላእክት አለቆቻቸውን ያከብራሉ፤ ለእነሱም ይታዘዛሉ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የመላእክት ሁሉ አለቃ ስለሆነ ከትእዛዙ አይወጡም፤ ሠራዊተ መላእክት የሚያከብሩትንና የሚታዘዙለትን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን እኛም እንደ ኢያሱ እናከብረዋለን እንታዘዘዋለን፡፡ መላእክትን ማክበርና መታዘዝ እንደሚገባ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡፡ <<በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ሥፍራ ያገባህ ዘንድ እነሆ እኔ መልአክህን በፊትህ እሰዳለሁ፤ በፊቱ ተጠንቀቁ፤ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት፤ አንተ ግን ቃሉን ብትሰማ፣ ያልሁህንም ሁሉ ብታደርግ፣ ጠላቶችህን እጣላቸዋለሁ፣ የሚያስጨንቁህንም አስጨንቃቸዋለሁ፣ መልአኬ በፊትህ ይሄዳልና…>>(ዘጸ.23÷20-22) በማለት ለሙሴ ተናግሯል፡፡ ይህ ቃል ለአንድ ጊዜ ብቻ ለሙሴና ለሕዝቡ ተነግሮ ያበቃ ሳይሆን እስከዛሬና ወደፊትም የሚቀጥል ነው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ✞✞✞ በስመ ሥላሴ ✞✞✞ † ♥ † እስጢፋኖስም ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ።† ♥ †(የሐዋ.ሥራ ፯፡፶፱-፷) እንኳን ለሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖ ወርሃዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን!!! † ♥ † ሰው ግን ዓለምን ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢጎዳ ምን ይረባዋል/ምን ይጠቅመዋል?† ♥ † ማቴ.፲፮፡፳፮ የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው። መዝ. 115/116፡15 † ♥ †እኔን የሚወድ ቢኖር እራሱን ይካድ መስቀሌንም ተሸክሞ /መከራዬን ሳይሰለች/ ዕለት ዕለት ይከተለኝ † ♥ †፡፡ ማቴ ፲፡፴፰-፵፪ † ♥ † ስለ ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ፣ እንዲሁም የሚሰደዱ ብጹዓን ይጠግባሉና፣ መጽናናትንም ያገኛሉና…† ♥ † ጌታ በተራራ ስብከቱ ከተናገራቸው፣ ካስተማራቸው የሕይወት ምግብ የሆነ ቃሉ ማቴ.፭፡፩-ፍጻሜ ቅዱስ እስጢፋኖስ በፍርድ አደባባይ ሲቆምና ሲከሠስ እውነቱን መናገሩ ሕይወቱን እንደሚያስከፍለው እያውቀ፡፡ እውነቱን መናገር አልፈራም፡፡ አያችሁ ቅዱስ እስጢፋኖስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ነበር ያስተዋለው፡፡ ውጤቱ ምንም ይሁን፡፡ እግዚአብሔር በእውነት የተሞላን እንድንሆን ይፈልጋል፡፡ የክርስቶስ ምስክር ሆነው የተሰዉት ቅዱሳን የክብር አክሊል የተቀዳጁት ለእውነት ስለሞቱ ነው፡፡ ነገር ግን በመንፈስ ሕያዋን ናቸው፡፡ በዘላለማዊ ደስታም ከእግዚአብሔር ጋር ኖረዋል፡፡ እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር። የነፃ ወጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር፤ ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም። በዚያን ጊዜ። በሙሴ ላይ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሡ። ሕዝቡንና ሽማግሌዎችንም ጻፎችንም አናደዱ፥ ቀርበውም ያዙት ወደ ሸንጎም አመጡትና። ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራ በሕግም ላይ የስድብን ነገር ለመናገር አይተውም፤ ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዓት ይለውጣል ሲል ሰምተነዋልና የሚሉ የሐሰት ምስክሮችን አቆሙ። በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት። ፮፡፰-፲፭) “ይህ እንዴት ያለ ይቅርታ ነው? ልክ ጌታ በዚያ በመከራ ሰዓት ብዙ መከራ ሲያጸኑበት አባት ሆይ የሚያደርጉት አያቁምና የቅር በላቸው ብሎ የፍቅር አምላክ ይቅርታ እንዳደረገላቸው ሁላ የጌታው ተከታይ የሆነው፤ እስጢፋኖስም።” “ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር። ተንበርክኮም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር።” (የሐዋ.ሥራ ፯፡፶፱-፷) የሰማዕቱ በረከት ይደርብን እስከ ሞት ድረስ ለአምላካችን እንድንታመን እርሱ ይርዳን፡፡ እስከ መጨረሻ ድረስ የታመንህ ሁን የህይወት አክሊል እሰጣሃለሁ ራዕይ 2፡10 ለዚህ ነው እኮ ቅ/ጳውሎስ “እሩጫዬን ጨርሻለሁ ሃይማኖቴን ጠብቄያለሁ ከእንግዲህ የሕይወት አክሊል ይጠብቀኛል” ያለው ፪ጢሞ.፬፡፮-፯ የእግዚአብሔር፣ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን ይቆየን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ለመስቀሉ ክቡር አሜን ። ይቆየን ጊዜ ሕዝበ እስራኤልን ፊት ፊት እየመራ ጠላቶቻቸው አሕዛብን አጥፍቶ ምድረ ርስትን ምድራዊት ኢየሩሳሌምን እንዳወረሳቸው ዛሬም ይኸው መልአክ ቅዱስ ማካኤል እስራኤል ዘነፍስ የተባልን ህዝበ ክርስቲያንን ፊት ፊት እየመራ ጠላቶቻችን ሠራዋተ አጋንንትን እያጠፋ ምድረ ርስት ወደተባለች ሰማየ ሰማያት ያገባናል፡፡ የእስራኤል ሕዝብ ታሪክ ለአዲስ ኪዳን ሕዝብ ምሳሌ ስለሆነ በታሪክነቱ ብቻ ተነግሮ የሚታለፍ አይደለም፡፡ ኦሪት ሰም ሲሆን ሐዲስ ኪዳን ደግሞ ወርቅ ነውና፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ያወጣ፣ በበረሃ 4ዐ ዓመት የመራቸው፣ ምድር ርስትን ያወረሳቸው መሆኑን በሌላ ስፍራ እንዲህ ይላል፡፡ ‹‹…በእስራኤል ሠራዊት ፊት ይሄድ የነበረው የእግዚአብሔር መልአክ ፈቀቅ ብሎ በኋላቸው ሄደ፤ የደመናውም ዓምድ ከፊታቸው ፊቀቅ ብሎ በኋላቸው ቆመ፡፡›› (ዘጸ.14÷15-20) በዚህ መሠረት እስራኤልን ይመራ የነበረው የእዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ እንዲሁም በኮሬብ ተራራ እግዚአብሔር ለሙሴ ሐመልማል ከነበልባል ተዋሕዶ በተገለጸለት ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል አልተለየም ነበር፡፡ (ዘጸ.3÷1-6፣ የሐዋ. 7÷30-34) በኦሪት የእግዚአብሔር መልአክ እየተባለ የሚጠራው አብዛኛውን ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያስተምራሉ በድርሳነ ሚካኤልም ተጽፎ ይገኛል፡፡ (መዝ.33÷7) ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ (ቅዱስ ሚካኤል) እግዚአብሔርን በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸዋል (በኢሳ.37÷36) ›› የእግዚአብሔር መልአክ(ቅዱስ ሚካኤል) መጣ፡፡ ከአሞራውያንም ሰፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ገደለ…›› በማለት ቅዱስ ሚካኤል ሕዝቅያስን እንዴት እንዳዳነው ተገልጿል፡፡ በአጠቃላይ ቅዱስ ሚካኤል ያልረዳው ቅዱስ የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በዳን.10÷13 ‹‹የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሃያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ›› በማለት የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት ተገልጿል /ዳን.10÷21/፡፡ በዚሁ በትንቢተ ዳንኤል ም.12÷1 ላይ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሳል በማለት ታላቅነቱን፤ለሰው ልጆች ሁሉ በአማላጅነቱና በተራዳኢነት የሚቆም እንደሆነ በማያሻማ ቃል ተገልጿል፡፡ ከዚህም ሌላ ዲያብሎስ ከነሠራዊቱ በእግዚአብሔር ላይ ባመፀ ጊዜ ከክብሩ ያዋረደው ወደምድር የጣለው ቅዱስ ሚካኤል ቅዱሳን መላእክትን በመምራት ከዲያብሎስና ከሠራዊቱ ጋር ስላደረገው ጦርነትና ስለተቀዳጀው ድል ቅዱስ ዮሐንስ እንዲሀ በማለት ገልጾታል፡፡ ‹‹በሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ፤ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ፡፡ አልቻላቸውምም፤ ከዚያም ወዲያ በሰማይ ሥፍራ አልተገኘላቸውም፡፡ ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው፡፡ ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀድሞው እባብ ወደ ምድር ተጣለ፡፡ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ…›› (ራእ.12÷7-9) ዛሬም ቅዱስ ሚካኤል ሰዳዴ አጋንት አጋንንትን የሚያሳድድ በመሆኑ ከሰይጣንና ከሠራዊቱ መከራ እንዲያድናቸው በጸሎት ለሚለምኑት በቃል ኪዳኑ ለሚማፀኑት ሁሉ ፈጥኖ እየደረሰ ይታደጋቸዋል፡፡ በዙሪያቸው እየከተመ አጥር ቅጥር ሆኖ ይጠብቃቸዋል፡፡ ከክፉ ነገር ሁሉ ያድናቸዋል (መዝ.33÷7)፡፡ በመልእክተ ይሁዳ ቁ.9 ‹‹የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር ጌታ ይገስጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም›› በማለት ቅዱስ ሚካአል ዲያበሎስን እንኳ እግዚአብሔር ይፍረድብህ ከማለት በቀር ሌላ ቃል አለመናገሩ ታጋሽነቱን ያሳያል፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ክብር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቅዱስ ሚካኤል ለማንም ያልተሰጠ እጅግ ታላቅ የሆነ ክብር እንደተሰጠው ተጽፎ እናገኛለን፡፡ ይኸውም በዕለተ ምጽአት ጌታችን ቅዱሳን መላእክትን አስከትሎ በክበበ ትስብአት በግርማ መለኮት በሚመጣበት ጊዜ ከእግዚአብሔር ዘንድ በሙታን ላይ ሥልጣን የተሰጠው ለዚሁ ለኃያሉ መልአክ ለቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ይህንንም ቅዱስ ጳውሎስ በሚገባ ገልጾታል፡፡ ‹‹እነሆ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ ሁላችን አናንቀላፋም፡፡ ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበተ ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋል፤ ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ፤ እኛም እንለወጣለን ይላል›› (1ቆሮ.15÷51-52) ከዚሁ ጋር በተጨማሪ ‹‹በጌታ ቃል የምንላችሁ ይህ ነውና እኛ ሕያዋን ሆነን ጌታ እስኪመጣ ድረስ የምንቀር ያንቀላፉትን አንቀድምም ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና በክርስቶስ የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ…›› (1ተሰ..4÷15-16) በማለት በዕለተ ምጽአት ምን ያህል ክብርና ጌትነት እንደሚሰጠው ይገልጽልናል፡፡ የቅዱስ ሚካኤል በዓል የቤተ ክርስቲያን አባቶች በየወሩ በ12 መታሰቢያውን እንድናደርግ አዘውናል፡፡ ይህንንም ያልቻለ በዓመት አራት ዐበይት በዓላትን ከቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ጀምሮ እንደተቻለ ማዝከር ይገባል፡፡ እነዚህም ኅዳር 12 ቀን ቀጥሎ ሰኔ 12 ቀን ከዚያም ነሐሴ 12 ቀንና ታኅሳስ 12 ቀን ናቸው፡፡ ከሁሉም የሚበልጠው ታላቁ በዓሉ ኅዳር 12 ቀን ነው፡፡ በዚህም ዕለት እግዚአብሔር በሰማይ ካሉ ሁሉ በላይ አድርጐ ሾመው፡፡ ስለትሕትናውና ስለ መታዘዙ ጌታውን ፈጣሪውን የከዳና የበጐ ሥራ ሁሉ ጠላት የሆነውን ሰይጣንን ድል ይነሣ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው፡፡ በዚህ ዕለት እንዲሁ ከላይ እንደተገለጸው ቅዱስ ሚካኤል በታላቅ ክብር ሆኖ በንጉሥ ጭፍራ አምሳል ለነዌ ልጅ ለኢያሱ የታየበት ዕለት ነው፡፡ በቅዳሴያችን ‹‹ተውህቦ ምሕረት ለሚካኤል፤ ለሚካኤል ምሕረት (ይቅርታ ርኀራኄ) ተሰጠው ይላል፡፡ ነቢዩ ሄኖክም ምሕረት ለሚካኤል መሰጠቱን ገልጿል፡፡ ትሕትናውን ታዛዥነቱን አስረድቷል (ሄኖክ. 6 ቁ.5 ምዕ.10 ቁ.12) ፡፡ የሰማያውያን ሠራዊት አለቃ ለሰው ሁሉ የሚራራና ስለ ሰው ልጆች ሳያቋርጥ ወደ ፈጣሪው የሚለምን ርኀሩኀ ትሑት የሆነው ኃያሉ ቅዱስ ሚካኤል የሠራውን ሥራ የክብሩን ገናንነት ጽፈን ለመጨረስ ስለማይቻለን በዚሁ እናበቃለን፡፡ ጸሎቱ እና በረከቱ፣ ተራዳኢነቱም ሀገራችንና ሕዝባችንን ይጠብቅልን አሜን፡፡ ድርሳነ ሚካኤል ዘየካቲት አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም። በየካቲት ወር በአሥራ ሁለት ቀን የሚነበብ ኃያል ክቡር የሚሆን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል ድርሳን ይህ ነው። ልመናው በረከቱ ከኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ከዚህ ነገር በኋላ በዚህ አገር የሚኖር ሃይማኖቱ የፀና አንድ ድሃ ነበር። በመዓልትም በሌሊትም ይጸልይ ነበር። ቅዱስ ሚካኤልን ጌታዬ ሆይ እዘንልኝ የዕለት ምግብ የዓመት ልብስ ስጠኝ ይለው ነበር። ሰውዬው ግን ሰነፍ ነው። ከቤቱ ወደሥራ አይወጣም ልድከም አይልም የሚያውቀው ሥራ የለም። አንዲት ሰዓት ስንኳ ልሥራ አይልም። ንግድም አያውቅም። ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በሕልም ተገልጦ ወደዚህ ደሃ ሰው መጣ። እንዲህም አለው።እርሻውም ቢሆን ንግድም ቢሆን ጥቂት ሥራ የማትወድ አንተ ሰነፍ ሰው በመዓልትም በሌሊትም ይቅር በለኝ እያልክ እንዴት ትለምነኛለህ። እባርክልህ ዘንድ ወይንህ የት ነው ስንዴህ የት ነው የሠራኸው የትነው የደከምክበት የት ነው። አንተ ሰነፍ ሰው የምተሸጠው የምትገዛበት የት አለ ጌታዬ ሚካኤል እዘንልኝ እንደምን ትለኛለህ። የደከምክበት ሥራ የት አለ። የሁሉ አባት አዳምን እግዚአብሔር እንዳለው አልሰማህምን፡ በክፉ በዲያብሎስ ሽንገላ የአዘዘውን ሕግ በተላለፈ ጊዜ። ይህች የተገኘህባት ምድር ናት ወደሷም ትመለሳለህ። ሥራ በፊትህ ወዝ እንጀራህን ብላ። እሾህ አሜከላ ይብቀልብህ አላለውምን አንተ ግን አትሠራም ግን ባርክልኝ ትለኛለህ። ይህን ብሎ ወደ ሰማይ ወጣ። በነጋ ጊዜም ይህ ድሃ ተነስቶ ሊጸልይ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደ። ሊጸልይም በቅዱስ ሚካኤል ስም ወደ ተሠራው መቅደስ ገባ። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ከኔ ጋር ሁን አትለየኝ አለ። ከቤተ ክርስቲያንም በወጣ ጊዜ እግዚአብሔርን የሚፈራ ለደሆች ለችገረኞች ብዙ ምጽዋት የሚሰጥ አንድ ባለጸጋ ሰው አገኘ። ይህ ድሃ ጌታዬ እዘንልኝ መቶ ወቄት ወርቅ ስጠኝ ሔጄ እነግድበት ራሴን እረዳበት ዘንድ ገንዘብህንም ከነወለዱ እከፍለሃለሁ አለው። ባለጸጋውም ድሃውን እኔ አላውቅህም ይህም ባይሆን ዛሬ ከዚህ ሀገር የሚዋስህ አንድ ሰው አምጣ። በኔና በአንተ መካከል ፀብ እንዳይሆን ገንዘቤን የሚመልስልኝ ዋስ ስጠኝ አለው። ይህም ድሃ ባለጸጋውን እኔ ድጋ ነኝና የሚዋሰኝ አላገኝም። አሁንም ፈቃድህ ከሆነ ከራራህልኝም ተነስተህ እኔም አንተም ሁለታችንም የመላእክት አለቃ ወደ ሚሆነ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እንሒድ እሱ አለቃዬ ነውና ይዋሰኛል አለው። ይህም ባለጸጋ አንተስ በቅዱስ ሚካኤል የምታምን ከሆነ እኔም አምንበታለሁና ተነሥ እንሒድ አለው። ከዚህ በኋላ ሁለቱም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ባለበት አንድነት ቆሙ። ይህም ደሃ የመላእክት አለቃ ጌታዬ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ስለዚህ ባለጻጋ አላመነኝምና አንተ ጌታዬ ተዋሰኝ አለው። ከዛሬ ጀምሮ በዓልህ እስከሚከበርበት ሰኔ አሥራ ሁለት ቀን ድረስ ለባለገንዘቡ ወርቁን እመልሳለሁ አለው። ይህም ባለጸጋ ነገርክን ሰማሁ ተነስ እንሂድ ልስጥህ አለው። ይህ ነገር ለባለጸጋው ድንቅ ሆኖበታልና። ከዚህ በኋላ ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ሁለቱም አንድነት ወደባለጸጋው ቤት ሔዱ። ባለጸጋውም መቶ ወቄት ወርቅ ሰጠው። ድሃውም የተሰጠውን ወቄት ወርቅ ይዞ ደስ እያለው ወደቤቱ ተመለሰ ከዚህም በኋላ ወደሮም አገር ሔደ በዚያ ወርቅም ነገደና አተረፈ። ከዚህ በኋላ ቀጠሮው የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል በዓል የሚሆንበት ዕለት ሰኔ አሥራ ሁለት ቀን እንደደረሰና ወደ ሀገሩ ሊመለስ እንዳልቻለ በአወቀ ጊዜ ጽኑ ኀዘን አዘነ። ተቆረቀረ። በልቡናውም አስቦ እንዲህ አለ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን ዋስ ያደረግሁበት ጊዜው ደረሰ ዛሬ መድረስ አልተቻለኝም ምን ላድርግ አለ። ያን ጊዜም የቅዱስ ሚካኤልን ተራዳኢነት የፈጣሪውንም ከሃሊነት አሰበ።ከዚህ በኋላ እጁን ወደ ሰማይ ዘርግቶ አንገቱን ወደ ላይ አቅንቶ ጸለየ። በፍጹም ልቡና በፀና ሃይማኖት ታምኖ ለባለ ዕዳው ከአምሳ ትርፍ ጋራ መቶውን ወቄት ወርቅ ይዞ በከረጢት ቋጥሮ በከረጢቱም ውስጥ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን ስምና የባለጸጋውን ስም ከነሱም ጋር የእሱን ስም ጻፈ። ከዚህ በኋላ ተነስቶ ወደ እንጥረኛ ሔዶ አንጥረኛውን የእርሳስ ሣጥን ሥራልኝ አለው። የእርሳስ ሣጥን ሠራለት። ከዚህ በኋላ ይህን ከረጢት ወስዶ ከውስጡ ጨምሮ ዘጋው። ከዚህ በኋላ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል በዓል ዋዜማ ቀን ወደ ወንዝ ሔደ ከባሕር ዳርም ቆሞ አቡነ ዘበሰማያት ደገመ እግዚአብሔርን ፈጽሞ አመሰገነ። በፍጹም ሃይማኖቱም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እነደተዋስከኝ ባለጠጋውና እኔ የተቃጠርንበት የበዓልህ ቀን ዛሬ እንደሆነ እኔም ከሩቅ አገር እንዳለሁ ዛሬም እስክንድርያ መድረስ እንዳይቻለኝ አንተ ታውቃለህ አሁንም የባለጠጋውን ገንዘብ ከነወለዱ ለአንተ ሰጥቼሃለሁ ለባለ ዕዳዬ መልስልኝ ብሎ ጸለየ ጸሎቱንም በጨረሰ ጊዜ ሣጥኑን ከነ መክፈቻው ወደ ባሕር ወረወረው ያን ጊዜ ጊዜውን ታላቅ ዓሣ ወጥቶ ሣጥኑን ተቀብሎ ዋጠው። ከዚህ በኋላ ያ ዓሣ በአንዲት ሌሊት የስድስት ወር ከስድስት ቀን ጎዳና ተጉዞ በነጋው ፀሐይ በወጣ ጊዜ ከእስክንድርያ ባሕር ወደብ ደረሰ። በዚች ቀን ያ ባለጸጋ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል በዓል ዓሣ ሊያሠግሩ ሔደው ከባሕር ላይ መረባቸውን ይጥሉ ዘንድ ብላቴኖቹን አዘዘ። ያ ዓሣ ተያዘና ወደ ባለ ጸጋው ወሰዱት ባለጠጋውም ባየው ጊዜ ደስ አለው ታላቅ ነበርና። ባለጠጋውም ብላቴኖችን ይህን ዓሣ ለበዓሉ ቅዱስ ሚካኤል አመጣልኝ አላቸው። ብላቴኖችን ያን ዓሣ ጥቡት ብሎ አዘዛቸው ሆዱንም በቀደዱት ጊዜ በዓሣው ሆድ ውስጥ ይህን የዋጠውን ሣጥን አገኙት። ያም ባለጸጋ ዕቃ ቤቱን በሀገራችን የተደረገውን በባሕርም ውስጥ የሆነውን ሁሉ ሰምተን እስክናውቅ ድረስ ይህን ሣጥን አስቀምጥ አለው። ከጥቂት ቀን በኋላ ያ ድሃ ወደ እስክንድርያ ከተማ ገባ። ባለዕዳውም አገኘውና ለምን እንዲህ አደረግህ አምኜ ገነዘቤን ብሰጥህ በጊዜው እንዴት አልሰጠኸኝም ለምንስ አልከፈልከኝም አለው። ያም ድሃ እኔስ ለተዋሰኝ ሰጥቼው ነበር በውኑ በቀጠሮው አልሰጠህምን አለው። ዋስህን ወዴት አግኝተኸው ሰጠኸው አለው ድኀውም እኔ ሩቅ አገር ስለ አለሁ የተቃጠረንበት ቀን በደረሰ ጊዜ ወደ አንተ መድርስ ባይቻለኝ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል በዓል ቀን መቶውን ወቄት ከአተረፍኩልህ ከአምሳ ትርፍ ጋር በከረጢት ውስጥ አድርጌ በላዩም የቅዱስ ሚካኤልን ስም የኔንና የአንተንም ስም ጽፌ በሣጥን ውስጥ አደርጌ ቆለፍኩና ያንንም ሣጥን ወስጄ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል በዓል ዋዜማ የመላእክት አለቃ ሚካኤል ሆይ እንደተዋስከኝ አንተ ታውቃለህ እነሆ እንካ ለባለ ዕዳዬ ገንዘቡን መልሰህ ሰጥልኝ ብዬ ከባሕር ጣልኩት አለው። ያ ድኀም ይህን ነገር በነገረው ጊዜ ባለጠጋው ከጥቂት ቀን በፊት የሆነውን ነገር አሰበና በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ቀን በዓሣው ሆድ ውስጥ የተኘገውን ሣጥን አምጣ ብሎ ዕቃ ቤቱን አዘዘው። አመጣለት በእጁም ይዞ ድኀውን ሣጥኔ ነው የምትለው ይህ ነውን አለው። ባለጠጋውም አዎን ጌታዬ አለው። ፈጥኖ ከፈተው። በከረጢቱ ላይም የቅዱስ ሚካኤልን ስምና የራሱንም ስም የባለጠጋውንም ስም እንደ ተጻፈ እንደ ታተመ አገኙ። መቶ ወቄትና ትርፉንም አምሳ ወቄት በውስጡ አገኙ። ስለዚህም ነገር ባለጸጋው የቅዱስ ሚካኤልን የተአምራቱን ገናንነት የአምላኩንም ከሀሊነት አደነቀ እግዚአብሔርንም አመሰገነ አከበረ ከፍ ከፍ አደረገ። መቶውን ወቄት ትርፉንም ይዞ ባለፀጋው ድሃውን እንዲህ አለው ወንድሜ ሆይ ሃይማኖትህ ፍጹም ነው። በእውነት አንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነህ ይህን ትርፍ ከአንተ አልቀበልም አለው። ያም ባለጸጋ ከገንዘቡ አምሳውን ወቄተ ወርቅ ወስዶ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ጽዋዕ አሠራው። ለመታሰቢያው ይሆነው ዘንድ ሁለቱም ከዚያን ቀን ጀምሮ እስከ ዕለተ ሞታቸው ወዳጅ ሆነው በእግዚአብሔር ፍቅር ፀንተው ኖሩ። ይህም ሁሉ የሆነው በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ነው። እኛንም በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል የጸሎት ኃይል እግዚአብሔር ይማረን ይቅር ይበለን በጥምቀት የተወለድን ሁላችንንም ይጠብቀን ለዘለዓለሙ አሜን። እሳታዊ ባሕርይ ያለው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ይህ ነው። ልመናው አማላጅነቱ ከኛ ጋር ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን። ቸር እግዚአብሔርን የሚፈራ አንድ ሰው እንደነበር ተነገረ። ለድኆች ለችግረኞች ቸርነትን ያደርግ ነበር። የአዳም ልጆች ሁሉ ባለጋራ በጎ ነገርን የሚጠላ ሰይጣንም ይህን ባየ ጊዜ ቀንቶ ጽኑ ደዌ አመጣበት። ሽባ ሆነ ጽኑ ደዌ ታመመ። ይህም ሰው ደዌው ስለጸናበት ሁል ጊዜ ይጮህ ነበር። ከደዌው ጽናት የተነሣ ከተኛበት መነሣት ተሳነው። ስለዚህም ዘመዶቹን ጎረቤቶቹን ወደመላእክት አለቃ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ከርስቲያን በሥውር ተሸክመው እንዲወስዱት ለመናቸው አንሱም ሰው ሳያውቅ በሌሊት ወሰዱት። እንደለመናቸውም የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል በአለበት ወስደው አስቀመጡት። ከዚህ በኋላ ያ ሰው በፍጹም ልቡና ወደ ቅዱስ ሚካኤል ይለምን ይማለል ይማልድ ጀመር። እንዲህ እያለ ጌታዬ የመላእከት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ በእግዚአብሔር ፊት በጸሎትህ አስበኝ ከአሁንም ና እርዳኝ። ከዚህ ከአገኘኝ ጽኑ ደዌም ፈውሰኝ አድነኝ እኔ አገልጋይህ ልመናህን አምኜ መታሰቢያህን ሳደርግ ኖሬአለሁና። ከልቅሶና ከጽኑ ዕንባ ጋረ ደረቱን እየመታ እንዲህ ሲል እኩለ ሌሊት በሆነ ጊዜ በላዩ ላይ ታላቅ ብርሃን ወጣ።የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከብርሃኑ ውስጥ ሆኖ እንዲህ ብሎ ተናገረው። ከዚህ ደዌህ እግዚአብሔር አድኖሃልና ከዚህ ደዌህ ዳን ተነሥ እነሆ እግዚአብሔር አድኖሃል ድኅነትንም ሰጥቶሃል እንግዲህ ዳግመኛ አትበድል ኃጢኣት አትሥራ ከዚህ የበለጠ እንዳያገኝህ። ይህንን ብሎት እጁን ዘርግቶ ሁለንተናውን ዳስሶ እግዚአብሔር ፈጽሞ አድኖሃልና ተነስተህ ሒድ አለው። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ቀንቶ በእግሩ ተነስቶ ሔደ። የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን ፈጣሪ እግዚአብሔርን እያመሰገነ።ከደዌው ስለ ዳነ ፈጽሞ ደስ አለው። በፍጹም ደስታ ቃል እያመሰገነ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት ሰገደ። ሕዝቡም ሁሉ ይህን ታላቅ ተአምራት ባዩ ጊዜ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን ክብር ገናንነት ፈጽመው አደነቁ። የተአምራቱን የነገሩን ምስጋና አበዙ። የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን ተአምር ያዩትም ለሰው ሁሉ ነገሩ። ያ የዳነው ሰውም ከቀድሞው ይልቅ በጎ ሥራን አበዛ። እስኪሞትም ድረስ በየወሩ በአሥራ ሁለት ቀን መታሰቢያ ማድረጉን አላስታጎለም። የቸርነትና የይቅርታ መልእክተኛ በሚሆን በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ገባ። እኛንም የክብር ባለቤት ጌታ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ከኃጢኣት ሞት ያድነን ከክፉ ቀን ከመከራ ዘመን ይሠውረን። መንግስተ ሰማያትን ያውርሰን። በዚህ ዓለም በሚመጣውም ዓለም የሕይወትን ተስፋ ያድለን አሜን። አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት አሥራ ሁለት ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል በዓል መታሰቢያ ነው። በዚች ቀን ክብር ምስጋና ይግባውና እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን የረዓይት ወገን ወደሚሆን ወደ ሶምሶን ልኮታልና። ሊገድሉት የፈለጉትን የፍልስጥኤምን ሰዎች ድል እስኪያደርጋቸው ድረስ ረድቶታልና። በእነሱ ላይ እግዚአብሔር ኃይል ሰጥቶት አጠፋቸው ከእነሱ በአንዲት ቀን በአህያ መንጋጋ ሺህ ሰው ገደለ። ውሃ ጠምቶት ሊሞት በደረሰ ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ታይቶ አፀናው ከአህያ መንጋጋ አጥንትም ውሃ አወጣለት ጠጥቶም ከውሃ ጥም ዳነ። የፍልስጥኤም ሰዎች ድል በሆኑ ጊዜ ከሚስቱ ጋር ተማክረው ዓይኑን አጥፍተው ወደ ጣኦታቸው ቤት ወሰዱት። የእግዚአብሔር መልእክተኛ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ታየው ተነጋገረው ኃይልንም ሰጠውና ሁሉንም አጠፋቸው ስለዚህ ነገር የቤተ ክርስቲያን መምህራን በየወሩ በአሥራ ሁለት ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል መታሰቢያ እናደርግ ዘንድ። አዝዘውናል። ልመናው ከእኛ ከሀገራችን ከኢትዮጵያ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
47836
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%94%E1%8B%B5%E1%8A%95%20%E1%8C%88%E1%8A%90%E1%89%B5
የዔድን ገነት
የዔድን ገነት (ዕብራይስጥ፦ /ገን ዐድን/) በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት እግዚአብሔር በሰው ልጅ መጀመርያ ቅድመ ታሪክ በምድር የተከለ ገነት ነበረ። ይህ ገነት በተለይ የሚገለጸው በኦሪት ዘፍጥረት 2 እና 3፣ እንዲሁም በመጽሐፈ ኩፋሌ 4 እና 5 ነው፤ ደግሞ በትንቢተ ሕዝቅያስ 28 ይጠቀሳል። አንዳንዴ በመሳሳት «ዔድን» ሳይሆን የ«ኤዶም» ገነት ተብሏል፤ ኤዶም ግን በትክክል የያዕቆብ ወንድም ዔሳው የመሠረተው ሀገር ነበረ። መጽሐፈ ኩፋሌ 4:14, 16 እንደሚያብራራልን፣ መጀመርዮቹ ሰዎች አዳም እና ሔዋን በገነት የቆዩበት ዘመን ሰባት አመታት ያህል ነበር። በመጽሐፈ ኩፋሌ አቆጣጠር አስርቱ ቃላት እስከ ተሰጡበት ዓመት ድረስ 2410 ዓመታት ስለሚቆጠር፣ እነዚህ ቅድመ ታሪካዊ ሰባት አመታት ከ4071 እስከ 4064 ዓክልበ. ያህል እንደ ነበሩ መረዳት ይቻላል። ሌሎች ግን በሌሎች ዘዴዎች በኩል ሌሎችን ፍቾች አገኝተዋል። አዳም ከተፈጠረበት ከሥነ-ፍጥረት 6ኛው ቀን ጀምሮ በአዳም 40ኛው ቀን ወደ ገነት እንደ ገባ፣ ሚስቱም ሔዋን በ80ኛው ቀን እንደ ገባች ይለናል ። ወደ ገነትም ሳይገቡ በተወለዱበት አገር በኤልዳ እየቆየ አዳም መጀመርያው ሳምንት እንስሶችን ያሰይማቸው ነበር፣ ከ፪ኛውም ሳምንት ጀምሮ ሔዋንን ያውቃት ነበር። አዳም ከተፈጠረበት ከዓለም 6ኛው «ቀን» አስቀድሞ ዓለሙ፣ ምድሩ፣ አትክልቱና እንስሶች ሁሉ ወዘተ. ተፈጥረው ነበር፤ እነዚህ 6ቱ «ቀኖች» ግን እንደ አሁን የ24 ሰዓት ቀኖች እንደ ነበሩ አይመስልም። በሥነ ቅርስ መጀመርያው የምናውቀው ታሪካዊ ሰነድ «የመንደሮቹ መኳያ ሰሌዳ» 3125-3100 ዓክልበ.ግ. ይመስላል፤ ከዚያ አስቀድሞ ለነበረው ዘመን የሰው ልጅ ታሪካዊ መዝገቦች (ሰነዶች) በፍጹም ባለመኖራቸው፣ ይህ ስለ «ቅድመ ታሪክ» አንድ ቅድመ-ታሪካዊ አስተያየት ሲሆን፣ በሰፊ በአብርሃማዊ ሃይማኖቶች (በተለይ ክርስትና፣ እስልምና፣ አይሁድና) የሚገኝ አስተያየት ነው። (ደግሞ ባለሙያ ንድፍን ይዩ።) በዚሁም አጭር የገነት ወቅት ከአሁን በጣም የተለዩ ሁናቴዎች እንደ ነበሩ የሚል አሣብ ይፈጠራል። አዳም እና ሔዋን በኤድን ሲቆዩ መዋቲ መሆናቸው እንደ ታሠበ አይመስልም። ሞት ለሰው ልጆች የመጣበት ምክንያት አዳም እና ሔዋን በዓመፃ ጸባይ የተከለከለውን ፍሬ ተመግበው ከዔድን ገነት ስለ ተሰደዱ እንደ ሆነ ይመስላል። የእንስሶች ጉዳይ በግልጽ ባይብራራልንም ከአዳም ጋር ለመናገር በዚሁ ወቅት ችሎታው እንደ ነበራቸው በኩፋሌ 5:2 ይጻፋል። እባብ በዚህ ሰዓት እግሮቹን ገና ስላላጣ ባለ እግር ፍጡር እንደ ነበር ይመስላል። የእግዚአብሔር መላእክት ለአዳምና ሔዋን የገነት አጠባበቅ በነዚህ 7 አመቶች ያስተምራቸው ነበር (ኩፋሌ 4:14)። «የአዳምና ሔዋን ትግል ከሠይጣን ጋራ» የአዳምና ሔዋን ትግል ከሠይጣን ጋራ ሌላ ቀኖናዊ ያልሆነ በተለይ በአረብኛና ግዕዝ የታወቀ ጥንታዊ ጽሑፍ ነው። በዚህ ጽሑፍ ዘንድ ግን አዳምና ሔዋን ሳይበድሉ በገነት የቆዩበት ወቅት ጥቂት ሰዓቶች ብቻ ነበር፤ ከገነትም በወጡ በ223ኛው ቀን (ወይም ከ7 ወርና 13 ቀናት በኋላ) አዳም ሔዋንን በጋብቻ ያገባት ነው። ይህ መረጃ ከኩፋሌ ጋር አይስማማም። ይኸውም መጽሐፍ ስለ ዔድን ገነት ተጨማሪ ዝርዝርዎች ይሰጣል። ከነዚህም መሃል፦ አዳም በገነት እያለ ሌሊትን አላወቀም ነበር። (እንደ ክፋሌ ለ፯ አመት እንዲህ ከሆነ የምድር ምኋር ከአሁን እንደ ተለየ መስሎ በገነት ምንጊዜም መዓልት ነበር ማለት ነው።) የገነት ፍሬ ከአሁን ትልቅ ነበር፤ በገነት ውስጥ አንድ የበለስ ፍሬ ክብደት እንደ አንድ ሃብሃብ ነበር። ጻዕሙም እንደ ጣፋጭ ሥጋ ወጥ ነበር። ወርቅ፣ ዕጣንና ከርቤም በገነት መኖራቸውም ይጠቀሳል። የተከለከለው ፍሬ እነዚህ ምንጮች የተከለከለውን ፍሬ መታወቂያ አይወስኑም። ብዙዎች እንደሚገመቱ የቱፋሕ ወይም የበለስ ዛፍ ነበረ። አንድ ሰነድ በጥንታዊ ስላቭኛ የተጠበቀው መጽሐፍ 3 ባሮክ እንዳለው፣ የተከለከለው ፍሬ ወይን ነበር። እግዚአብሐር የእባቡን ባሕርይ እንደ ለወጠ ሁሉ የወይኑንም ባሕርይ በቅጣቱ ከዛፍ ወደ ሐረግ ብቻ ለወጠ ይላል። ሆኖም በእቅዱ ወደፊት የመድኃኔ አለም ደም በመሆኑ ከእርጉም ወደ በረከት ይለውጠዋል በማለት ተጨመረ። በመጽሐፍ ቅዱስና ሌሎች ምንጮች ስለ ገነቱ ሥፍራ አንዳንድ ፍንጭ ይሰጣል፤ ስለ ፍንጮቹ ትርጓሜ ግን አስተሳሰቦች ተለይተዋል። «እግዚአብሔር አምላክ በምሥራቅ በኤድን ገነትን ተከለ... ወንዝም ገነትን ያጠጣ ዘንድ ከዔድን ይወጣ ነበር፤ ከዚያም ለአራት ክፍል ይከፈል ነበር። የአንደኛው ወንዝ ስም ፊሶን ነው፤ እርሱም ወርቅ የሚገኝበትን የኤውላጥ ምድርን ይከብባል፤ የዚያም ምድር ወርቅ ጥሩ ነው፤ ከዚያም ሉልና የከበረ ድንጋይ ይገኛል። የሁለተኛው ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል። የሦስተኛውም ወንዝ ስም ጤግሮስ ነው፤ እርሱም በአሦር ምሥራቅ የሚሄድ ነው። አራተኛውም ወንዝ ኤፍራጥስ ነው።» (ዘፍ. 2:8, 10-14) በዚህ ጥንታዊ ወቅት የነበረው መልክዓምድር ከአሁኑ እንደ ተለየ ይመስላል። ከተጠቀሱት ወንዞች፣ የጤግሮስና የኤፍራጥስ መታወቂያዎች ያለ ክርክር ታውቀዋል። «ግዮን» የአባይ (ናይል) ስም ሲሆን ኢትዮጵያንም ይከብባል። የ«ፊሶን» ሥፍራ በተለይ አጠያያቂ ሆኗል፣ ኤውላጥ ግን በኋላ የኖህ ልጆች ዘመን ስሙን ለአገሩ ሰጠ፤ በአረቢያ በቀይ ባሕር አጠገብ እንደ ተገኘ ይታስባል። ቀይ ባሕሩ በዚህ ወቅት ወንዝ ብቻ ከሆነ፣ እሱ የፊሶን መታወቂያ ሊሆን ይቻላል፤ ወይም የሕንድ ሥፍራ ያንጊዜ በአፍሪካና በአረቢያ አጠገብ ከሆነ፣ የፊሶን መታወቂያ ሌሎች እንደሚሉ ሕንዱስ ወንዝ ሊሆን ይቻላል። አባይ ደግሞ ወደ ሜድትራኔያን ባህር ሳይፈስ ወደ ዔድን ለመድረስ በሲናና ዮርዳኖስ በኩል እንደ ተዛወረ ይመስላል። በዕብራይስጥ ትርጉሙ፣ በኢትዮጵያ ሥፍራ «ኩሽ» አለው፤ በአንዳንድ ምዕራባውያን ሊቃውንት ሃልዮ ዘንድ ይህ «ኩሽ» ኢትዮጵያ ሳይሆን በ1500-1100 ዓክልበ. ግድም ባቢሎንን የገዙት ብሔር «ካሣውያን» ይሆናሉ ብለዋል። በኩፋሌ 9፣ የገነቱ ሥፍራ በሴም ርስት ውስጥ፣ ለካም ርስት ቅርብ መገኘቱ ይመስላል። በተለይም በ9:8 ዘንድ ገነት፣ ደብረ ሲናና ደብረ ጽዮን ሦስቱ ቅዱስ ቦታዎች «አንዱ በአንዱ አንጻር ለምስጋና ተፈጠሩ» ይለናል። ሄኖክ ሳይሞት መላእክት ወደ ገነት እንዲመለስ ፈቀዱ በምዕራፍ ፭ ሲለን፣ አራተኛው የተቀደሠ ቦታ «የምሥራቁ ደብር» ይባላል፤ ይህ ደብረ አራራት መሆኑ ይታስባል። በተቀበልነው ትርጉም በዘፍጥረት ዘንድ አዳምና ሔዋን ከኤድን ወደ ምሥራቅ ተሰደዱ፤ በኩፋሌ ወደ ተፈጠሩበት ወደ ኤልዳ (ወይም «ሞኤልዳ») ተመለሱ፤ ባብዛኞች ጥንታዊ ምንጮች ይህ ከገነት ወደ ምዕራቡ ተገኘ። ወንዞቹ ሁሉ በዚያን ጊዜ የተጋጠሙበት ምድር አሁን የአረብ በረሃ ቢመስልም፣ በመስጴጦምያ ወይም በአፍሪካ እንደ ነበር የሚሉ ብዙ አሉ። እንዲሁም ሌሎች በጣም ልዩ ልዩ አስተሳስቦች አሉ። ለምሳሌ በሞርሞኒስም ዘንድ፣ የዔድን ገነትና የአዳምና ሔዋን ዕውነተኛ መገኛ በሚዙሪ ክፍላገር አሜሪካ ነበረ። መጽሐፍ ቅዱስ
45686
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8A%9B%20%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%88%9D%E1%88%B3%E1%88%8C%E1%8B%8E%E1%89%BD
አማርኛ ተረት ምሳሌዎች
"ሁለት ጊዜ በላህ ተፋህ ሁለት ጊዜ ተናገርህ ከፋህ" ሁለት ጊዜ ነው የዶሮ ልደት አንዱ በእንቁላል አንዱ በጫጩት ሁለት ጊዜ ይፈርዱ ጉድ ይወልዱ ሁለት ጥፉ ካገር ይጥፉ ሁሉ ሄደ ተበተነ እህና እኔ ቀረነ አለ ያዘነ ሁሉ ሆነ ቃልቻ ማን ይሸከም ስልቻ ሁሉ በእጄ ሁሉ በደጄ ሁሉ ቢናገር ማን ይሰማል ሁሉ አማረሽን ዲስኮ () አታውጧት ሁሉ አማረሽን ገበያ አታውጧት ሁሉ አማረኝን ገበያ አታውጣት ሁሉ አረሰ ማን ይሸምት ሁሉ የሚገኝ ከእሱ የሚገኝ የለም ያለእርሱ ሁሉ ያልፋል እስኪያልፍ ያለፋል ሁሉ ያልፋል እውነት ብቻ ይተርፋል ሁሉም ሰው መምሰሉ ባይታይ አመሉ ሁሉም ሸክሙን ፍቅርም ያዥውን ሁሉም በየዘመድህ ቢሉት አክንባሎ ጋጥ ገባ ሁሉም በየዘርህ ቢሉት አከንባሎ ጋጣ ገባ ሁሉም አካል ነው ግን እንደአይን አይሆንም ሁሉም ከልኩ አያልፍም ሁሉም ከኋላው ያገኘዋል እንደስራው ሁሉም ወንፈሉን ፈታይም ድውሩን ሁሉም ያልፋል እውነት ብቻ ይተርፋል ሁሉም ያልፋል የሚኮርጅም ቢሆን ሁሉም ያልፋል ግን እስኪያልፍ ያለፋል ሁሉን ለእኔ አትበል ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል ሁሉን አውቆ አሳውን እሾህ ከስጋው ለይቶ ሁል ጊዜ ባሬራ ትበያለሽ ወይ አንዳንድ ጊዜ እንኳ ወጥ አትይሞይ ሁል ጊዜ ከመደንገጥ አንድ ጊዜ መሸጥ ሂዳ ጉበት ቢነሷት ታናሽ ታላቅ ስደዱልኝ አለች ሂዳ ጉበት የነሷት ታናሽ ታላቅ ስደዱልኝ አለች ሂዳ ጉበት ይነሷታል ታናሽ ታላቅ ላኩልኝ አለች ሂድ አትበለው እንደሚሄድ አርገው ሂድ አትበለው እንዲሄድ አድርገው ሂድ ካገር ኑር ካገር ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም ህልም አለ ተብሎ ሳይተኛ አይታደርም ህመሙ ቀርቶ ሞቱን በሰጠኝ ህመሙ ቀርቶ ሞቱን በተወኝ ህመሙን የሸሸገ መድሀኒት የለውም ህመሙን የደበቀ መድሀኒቱም አልታወቀ ህመሙን የደበቀ መድሀኒት የለውም ህያዋን ለነገስታት ሙታን ለካህናት ይገብራሉ ህዳር መማረሪያ ሰኔ መቃጠሪያ ህግ ይኖራል ተተክሎ ስርአት ይኖራል ተዛውሮ ሆሆሆ ስቄ ልሙት አለ ሰውየው ሆቴል ቢያብር ገንዘብ ያስገኛል ሆደ ሰፊ ነገር አሳላፊ ሆደ ሰፊ ይሻላል ከአኩራፊ ሆዱ ሲሞላ ፍቅሩ ሌላ ሆዱ ሲጎድል ሰው ያጋድል ሆዱ ናረት ሙያው ከጅረት ሆዱ ወድዶ አፉ ክዶ ክፉ ለምዶ ሆዱ ፈሪ እግሩ ዳተኛ አዳም ሲዋጋ እርሱ ይተኛ ሆዱን የወደደ ማእረጉን የጠላ ሆዱን የወደደ ማእረጉን ይጠላል ሆዱን ያለ ሆዱን ተወጋ ሆዳም ሰው እንብርት የለውም ሆዳም ቢሸከም የበላ ይመስለዋል ሆዳም ቢፈተፍት የጠገበ ይመስለዋል ሆዳም ፍቅር አያውቅም ሆዴ ሆዴ የሚለውን ጌታ ያየዋል አይኔ አይኔ የሚለውን ሰው ያየዋል ሆዴ በጀርባዬ ቢሆን ገፍቶ ገደል በጣለኝ ሆዴ ኑር በዘዴ ሆዴ አታጣላኝ ከዘመዴ ሆዴን በልቶኝ ጎኔን ቢያኩኝ አይገባኝ ሆድ ሆዴን የምትል ወፍ አለች ምናለች ሆድ ለማታ በልቶ ለጠዋት ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ሆድ ለባሰው ቢላዋ አታውሰው ሆድ ለተተባሰው ማጭድ አታውሰው ሆድ ሲሞላ ራስ ባዶ ይቀራል ሆድ ሲያር ጥርስ ይስቃል ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ጠዋት ሆድ ባዶ ይጠላል ሆድ ባዶን ይጠላል ሆድ እንዳሳዩት ነው ሆድ ከሁዳድ ይስፋል ሆድ ካገር ይስፋል ሆድ ወዶ አፍ ክዶ ክፉ ለምዶ ሆድ ዘመድ ሳይወድ አፍ እህል ሳይለምድ ሆድ የሸሸገውን ብቅል ያወጣዋል ሆድ የኔ ነው ሲሉት ቁርጠት ሆኖ ይገድላል ሆድ ያበላውን ያመሰገናል ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል ሆድህን ጎመን ሙላው ጀርባህን ለጠላት አታሳየው ሆድና ግንባር አይሸሸጉም ሆድና ግንባር አይሸሸግም ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግማል ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት ዳገት ላይ ይለግማል ለሀምሳ ጋን አንድ አሎሎ ይበቃል ለሀብት መትጋት ሰውነትን ያከሳል ገንዘብን ማሰብ እንቅልፍ ይነሳል ለሀጥአን የወረደ ለጻድቃን ይተርፋል ለሁሉም ጊዜ አለው ለሂያጅ የለውም ወዳጅ ለህልም ምሳሌ የለውም ለሆዳም ሰው ማብላት ውቅያኖስን ለመደልደል መቃጣት ለሆዳም በሬ ገለባ ያዝለታል ለሆዳም በሬ ጭድ ያዝለታል ለሆዳም በሬ ቫት ተከፈለ ለሆዳም በቅሎ ጭድ ያዝለታል ለሆዴ ጠግቤ በልብሴ አንግቤ ለሆድ ቁርጠት ብላበት ለራስ ምታት ጩህበት ለላሙ መንጃ ለሸማው መቅደጃ ለላሙ መንጃ ለሸማው መከንጃ ለላም ቀንዷ አይከብዳትም ለላም ከጥጃዋና ከአላቢዋ ማን ይቀርባታል ለላም የሳር ለምለም ለላም ጥጃዋ ለአህያ ውርንጭላዋ ለሌለው ምን ትለው ለሌባ ቅሌት ልብሱ ነው ለልደት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ ለልጅ ሲሉ ይበሉ ለወዳጅ ሲሉ ይጠሉ ለልጅ ሲሉ ይበሉ ለወገን ሲሉ ይጠሉ ለልጅ አይስቁለትም ለውሻ አይሮጡለትም ለልጅ ከሳቁለት ለውሻ ከሮጡለት ለልጅ ጥርስህን ለዝንብ ቁስልህን ለልጅ ጨዋታ ለባለጌ ቧልታ ለሎሌው ምን ትለው ለመሀን እምዬ ለአገልጋይ እትዬ ብርቋ ነው ለመሄድና ለመላወስ አዛዥ ራስ ለመሄድና ለመመለስ አዛዥ ራስ ለመሆኑ ሳይሆን እንዴት ይሆናል ቢሆን ለመማር ክፍል መግባት ለመኮረጅ ካሮት መብላት ለመማር ክፍል መግባት ለማለፍ ካሮት መብላት ለመስማት የፈጠንህ ለመናገርና ለቁጣ የዘገየህ ሁን ለመስማት የፈጠንህ ለመናገር የዘገየህ ሁን ለመስራት የሚያፍር መብላት አይደፍርም ለመስራት ያፈረ ለመብላት ደፈረ ለመስጠት አለመቸኮል ከሰጡም ወዲያ አለመጸጸት ለመነኩሴ መልካም ሎሌ ለመታማት መፍራት ለመከራ ያለው መነኩሴ ዳዊቱን ሸጦ አህያ ይገዛል ለመከራ የጣፈው ቢነግድ አይተርፈው ለሙት የለው መብት ለሚመለከት ለሚያየው ሞት ቅርብ ነው ለሚስት ያጎርሷል ለተመታ ይክሷል ለማረም ማን ብሎት ሲሰራው ግን ግድፈት ለማን አለው ፈጣሪ አለው ጠጅ ለሌለው ውሀ አለው ለማን ይፈርዱ ለወደዱ አይደለም ለወለዱ ለማኝ ቢያብድ ስልቻውን አይጥልም ለማኝ አያማርጥም ማር አይኮመጥጥም ለማየት የፈለገ አይኑን ይገልጣል ለማያቅህ ታጠን ብሎሀል ሀሰን ለማያውቅ ፎገራ ዱሩ ነው ለማያውቁሽ ታጠኚ ለማያውቁሽ ታጥበሽ ቅረቢ ለማይሞት መድሀኒት አለው ለማይሰጥ ሰው ስጡኝ ማለትን ማን አስተማረው ለማይሰጥ ሰው ስጡኝን ማን አስተማረው ለማእበል ወደብ ለነፋስ ገደብ የለውም ለምሽት መብራት ለመከራ ጊዜ ብልሀት ለምክንያት ምክንያት አለው ለምን ላለው ፈጣሪ አለው ጠጅ ለሌለው ውሃ አለው ለምን ሰርግ ይሄዳል ሰርግ አለ በቤቱ ለምን ተክዤ አምላክን ይዤ ለምን ያለው ስልቻውን ጫን ያለው ኮርቻውን ለምን ያለው ስልቻውን ጫን ያለው ኮርቻውን አያጣም ለምን ጊዜው ነቀዝሽ ለምኖ ለማኝ ቆቤን ቀማኝ ለሞኝ ሰኔ በጋው መስከረም ክረምቱ ለሞኝ ንገረው ምን ይሰማ ብዬ ለብልህ ንገረው ምን ይሳተው ብዬ ለሞኝ ከሳቁለት ለውሻ ከሮጡለት ለሞኝ ጉድጓድ አያሳዩትም ቤት ነው ብሎ ይገባበታል ለሞፈር ቆራጭ እርፍ አይታየውም በግላጭ ለረዥም ሰው ልብ እና ልብስ ያጥረዋል ለረዥም መንገድ አትሩጥበት ለረዥም ነገር አትቸኩልበት ለራሱ አያውቅ ነዳይ ቅቤ ለመነ ላዋይ ለራሱ አያውቅ ጠንቋይ መድሀኒቱ ላዋይ ለራሱ ጥላ ለእግሩ ከለላ ለራሱ የማይረባ ለሌላም አይረባ ለራሱ የማይረባ ለሰውም አይረባ ለራስ ምታት ጩህበት ለሆድ ቁርጠት ብላበት ለራሱ አያውቅ ሰው አይጠይቅ ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ ለራስ ቢያወሩ ለቅንቅን ይዘሩ ለራስ ቢያወሩ ለቅንቅን ይዘሩ አለች ዶሮ ለራስ ከበጁ አይታጡ ደጁ ለራበው ሰው ቆሎ ለቁልቁለት በቅሎ ለራበው ባዶ መሶብ ማቅረብ ለራት የማይተርፍ ዳረጎት ለርስት ሴቶች ስንኳ ይሞቱበታል ለሰማይ ምሰሶ የለው ለባእድ ስር የለው ለሰለባ የመጣ ልብስ ቢጥሉለት አይመለስ ለሰለባ የመጣ ልብስ ቢጥሉለት አይመለስም ለሰበበኛ ቂጥ መረቅ አታብዛበት ለሰባቂ ጆሮህን አትስጠው ለሰው ልጅ ሲያበሉ ለውሻ ልጅ ያብሉ ለሰው ልጅ ከሚያበሉ ለውሻ ልጅ ያብሉ ለሰው ልጅ ከማብላት ለውሻ ልጅ ማብላት ለሰው ልጅ እውቀት ለጦጣ ብልጠት ለሰው ሞት አነሰው ለሰው ሞት አነሰው ውሻውንስ ፈሴ መለሰው አለች ቀበሮ ለሰው ቢነግሩት ለሰው ለሰው ቢናገሩ መልሶ ለሰው ጫር ጫር አድርጌ አፈር ላልብሰው ለሰው ብሎ መሞት አምላክነት ያሻል ለሰው ብሎ ሲያማ ለኔ ብለህ ስማ ለሰው ብትል ትጠፋለህ ለእግዜር ብትል ትለማለህ ለሰው እንግዳ ላገሩ ባዳ ለሰው እንዴት አነሰው ለሰው ከበሬታው ሰው ለወጥ ማጣፈጫው ጨው ለሰው ጠላቱ ይወጣል ከቤቱ ለሰው የማይል ሰው ሞትም ሲያንሰው ለሰው ብሎ ሲያማ ለእኔ ብለህ ስማ ለሴትና ለጉም አይዘነጉም ለሰይጣን አትስጠው ስልጣን ለእሳት ውሀ ለጸጉር ቡሀ ለሴት ልጅ እስከአርባ ቀን ሞቷን ከዚያ ወዲያ ሀብቷን ለሴት ምስጢር ማውራት በወንፊት መቅዳት ለሴት ምክር አይገባትም ለሴትና ለጉም አይዘነጉም ለሴት ጠላ ለፈረስ ቆላ ለስሟ መጠሪያ ቁና ሰፋች ለስሱ ፍትፍት አሳይቶ እበት ያጎርሷል ለሸማኔ ማገጃ ስለት ማረጃ ለሹመት ካልመከሩለት ለጥርስ ካልነከሩለት ለሹመት ካልመከሩለት ለጥርስ ካልከደኑለት ለሹመት ያደለው የለማኝ አለቃ ይሆናል ለሺ ፍልጥ ማሰሪያው ልጥ ለቀላል ምስጢር መንገር በቀዳዳ ጤፍ መቋጠር ለቀላል ሰው ምስጢር መንገር በቀዳዳ ጤፍ መቋጠር ለቀላል ሰው ምስጢር መንገር በቀዳዳ አቁማዳ ጤፍ መቋጠር ለቀማኛ የለውም እጅ ለበቅሎ የለውም ልጅ ለቀበጠች አማት ሲሶ በትር አላት ለቀባሪው አረዱት ለቀን ቀጠሮ ለሴት ወይዘሮ ለቀንዳም በሬ ቤት አትከልክለው ቀንዱ ይከልክለው ለቀንዳም በሬ ቤት አትከልክለው ቀንዱ ይከለክለዋል ለቁንጫ ለምጽ ያወጣል ለቁንጫ መላላጫ ለቂጡ ጨርቅ የለው ቆንጆ ያባብላል ለቅልብልብ አማት ሲሶ በትር አላት ለቅሶ ሳለ ከቤት ይሄዳል ጎረቤት ለቅናት የለውም ጥናት ለቅዘን እግር አንስተውለት ለውሻ ሮጠውለት ለቆመ ሰማይ ቅርቡ ነው ለቆማጣ አንድ ጣት ብርቁ ናት ለበራ ወለባ ለውሻ ገለባ ለበጋ ጥጃ ውስ አነሰው ወይ ለበግ ደጋ ለምቾት አልጋ ለቡናሽ ቁርስ የለሽ ለነገርሽ ለዛ የለሽ ለባለጌ ገድሉ ውርደቱ ለቤት ሳማ ለውጭ ቄጤማ ለቤት ሳንቃ ለሰው አለቃ ለቤት ሳንቃ ለነገር ጠበቃ ለቤት ባላ ለችግር ነጠላ ለብልህ ንገረው ምን ይስተው ብዬ ለሞኝ ንገረው ምን ይገባው ብዬ ለብልህ አይነግሩ ለድመት አያበሩ ለብልህ አይነግሩ ላንበሳ አይመትሩ ለብልህ አይነግሩ ለንጉስ አይመክሩ ለብልህ አይነግሩም ለንጉስ አይመክሩም ለብልህ አይነግሩ ካልጠየቀ በስተቀር ለተማሪ ቆሎ ለወታደር በቅሎ ለተሟጋች መዘዘኛ የዳኛ ትእግስተኛ ለተረታው ያበደረ እሳት ጨመረ ለተራበ ግብር ለተበደለ ነገር ለተራበ በግብር ለተበደለ በነገር ለተራበ ቂጣ ለተጠማ ዋንጫ ለተሸሸገ ምግብ የተሸሸገ ሆድ አይጠፋለትም ለተሾመ ይሟገቱለታል ለተሻረ ይመሰክሩበታል ለተሾመው ይመሰክሩለታል ለተሻረው ይመሰክሩበታል ለተሾመ ይመሰክሩለታል ለተሻረ ይመሰክሩበታል ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ ነው ለተባባሰው ማጭድ አታውሰው ለተንኮለኛ ሲሉ ይሰበስባሉ ለቅን ይፈርዳሉ ለተወገረ የማያዝን እንብርት የለውም ለትኋን ልጓም ማጉረስ ላፈኛ ሰው መመለስ ለትኋን ልጓም ማጉረስ ላፈኛ ሰው መመለስ አይቻልም ለቸኮለ ሰው ዋንጫ አስጨብጠው ለችግር የፈጠረው ቢነግድ አይተርፈው ለነገረኛ ሰው ጀርባህን ስጠው ለነገረኛ ነገር ተውለት ለሆዳም እህል አቅርብለት ለኔ ነግ በኔ ለንጉስ የማይገዛ ለእግዚአብሄር አይገዛ ለንጉስ ያልረዳ ከባህር የማይቀዳ ለንጉስ ያልረዳ ከባህር ያልቀዳ ለንፉግ ሰው የገበያ መንገድ ይጠበዋል ለንፉግ ሰው የገበያ መንገድ ይጠበው ለአህያ ማር አይጥማትም ለአምላክ ልንገረው ለማያስቀረው ለአበባ የለው ገለባ ለአቤቱታ የለው ይሉኝታ ለአንበሳ አታበድር ካበደርክ አትጠይቅ ለአንተ ያለውን እንጀራ ይሻግታል እንጂ ማንም አይበላውም ለአኩራፊ ምሳው እራት ይሆነዋል ለአይነ ስውር መስተዋት ለአይንና ለወዳጅ ጥቂት ይበቃል ለአይን የሚከፋ ለአፍንጫ ይከረፋ ለአዋጅ ነጋሪት ለጥጥ ልቃቂት ለአገሩ እንግዳ ለሰው ባዳ ለአፈ ግም አፍንጫ ድፍን ያዝለታል ለአፉ ለከት የለውም ለአፍታ የለውም ፋታ ለአፍ ዳገት የለውም ለእሳት እንጨት ካልነሱት አይጠፋም ለእሳት እንጨት ካልነፈጉት አይጠፋም ለእሳት ውሀ ለጸጉር ቡሀ ለእሳት ፍላት ለጮማ ስባት ለእበጥ ፍላት ለእንጨት እሳት ለእባብ እግር የለው ለሞኝ መላ የለው ለእብለት ስር የለው ለእባብ እግር የለው ለእብለት ስር የለውም ለእባብ እግር የለውም ለእበጥ ፍላት ለእንጨት እሳት ለእኔ እናት ምን ደላት ያም አፈር ያም ድንጋይ ጫነባት ለእውር ዝማሜ ለመላጣ ጋሜ ለእጅ ርቆ ለአይን ጠልቆ ለእግሩ የተጠየፈ ለቂጡ አተረፈ ለእግር የፈሩት ለቂጥ ይተርፋል ለእግዚአብሄር የቀነቀነ ለጽድቅ ለጌታ የቀነቀነ ለወርቅ ለእውነት ማማ ለውሸት ጨለማ ለከለላ ጥላ ቢርብህ ብላ ለከሳሽ የለው መላሽ ለካህን ጥምቀት ለገበሬ ግንቦት ለክፋት ያደለው አሳዳጊ የበደለው ለኮ መሳቢያ ወፍጮ ማላሚያ ለወሬ ሞትሁ ለወሬ ሞትሁ ለእህል ሰለፍኩ ለወሬ ወዳጁ ወሬ ለመነኩሴ ጥሬ ለወሬ የለው ፍሬ ለወሬ የለው ፍሬ ለአበባ የለው ገለባ ለወሬ የቸኮለ እናቱን በመንገድ ይረዳል ለወርቅ ያሉት አንገት ላሽክት ለወታደር ሰፊ መንደር ለወዲላ መልካም ዱላ ለወይዘሮ መልካም ዶሮ ለወደላ መልካም ዱላ ለወዳጅ የማር ወለላ ለጠላት አሜኬላ ለወዳጅና ለአይን ትንሽ ይበቃዋል ለወጡም እዘኑለት ከእንጀራውም ጉረሱለት ለወጡ ጊዜስ ከደረቁም ለወጡም እዘኑለት ከደረቁም ብሉለት ለወጥ የሚሻል ቅልውጥ ለዋንጫ ቡሽ ለውሀ ጉሽ የለውም ለዋስ አፍ የለው ለጉንዳን ደም የለው ለውሻ ምሳ የለው ራት ብቻ ለውሻ ሞት ፊት አይነጩለትም ለውሻዬ ያልሁትን ልጄ ቢበላብኝ አልወድም ለውሽማ ሞት ፊት አይነጩለትም ለውጡኝ ባይ የሚሻለውን አውቆ ለዘመዴ ያዝናል ሆዴ ለዚህ ሆዴ ጠላኝ ዘመዴ ለዝናም ጌታ ውሀ ነሱ ለዝናም ጌታ ውሀ ነሱት ለዝንብ ከትላንት ወዲያም ድሮ ነው ለይቶ እንደፈፋ አንጓሎ እንዳረፋ ለይቶት አባ ንጉሷ ለደህና ሰው ዋጋ አነሰው ለደህና ሰው ውሸት ለጅብ እሸት ለደብተራ መቋሚያና ጭራ ለደደብ ማስረዳት ድንጋይ ቅቤ መቀባት ለደግ ንጉስ እለት እለት ማልቀስ ለዳርቻው ሲሳሱ መካከሉን ተነሱ ለዳርቻው ሲሳሱ ከነመሀሉም ተነሱ ለዳባ ለባሽ ነገርህን አታበላሽ ለዳኛ አመልክት እንዲሆን መሰረት ለዳኛ የነገሩት በርጥብ ያቃጠሉት ለዳኛ ዳኛ አለው ለአንበሳ ተኩላ አለው ለድሀ ማን ሰጠው ውሀ ለድህነት የፈጠረው ቢነግድ አይተርፈው ለድህነት የፈጠረው ቢነግድ አያተርፍም ለድሪ ያሉት አንገት ለአሸንክታብ ለድሪ ያሉት አንገት ላሽክት ለድካም የጣፈኝ ብነግድ አይተርፈኝ ለዶሮ ሲነገሩ ምጥማጥ ይሰማል ለጆሮ ጥርስ ለሆዳም ስስ ለገላጋይ ደም የለውም ለገበሬ መልካም በሬ ለገቢህ ተንገብገብ ለገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ ለገደለ ጎፈሬ ላረጋገጠ ወሬ ለገዳም የረዳ አይጎዳ ለጉንዳን ደም የለው ለዝንብ ቤት የለው ለጉንዳን ደም የለው ለገንዘብ ቤት የለው ለጋስ ቢለግስ አበደረ እንጂ አልሰጠም ለጋስ ቢለግስ አበደረ እንጂ እንዲያው አልሰጠም ለእግዜር የተቀናቀነ ጽድቅ ለንጉስ የተቀናቀነ ወርቅ ለጎበዝ ስጠው ሰንጋ ፈረስ ለጠላትህ እንደ ዳቦ እስኪገምጥህ አትመቸው ለጠቢብ አንድ ቃል ይበቃል ለጠጪ ሰው የመጠጥ ወሬ አውራው ለጥልና ለዳኛ ያለው ገንዘብ አፋፍ ይቆያል ለጥርጣሬ ምንጣሬ ለጥቅም ሲታጠቁ ከጎን ይጠንቀቁ ለጥቅምት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ ለውጠኝ ባይ የሚሻለውን አውቆ ለጨለማ ጊዜ መብራት ለመከራ ጊዜ ብልሀት ለጨቅጫቃ ሰው ከማበደር ይሻላል በጄ ማደር ለጭሰኛ መሬት ለሳር ቤት ክብሪት ለጾም ግድፈት ለበአል ሽረት ለጾም ግድፈት ለባል ሽረት ለፈረስህ አንገት ለጋሻህ እንብርት ለፈሪና ለንፉግ እያደር ይቆጨዋል ለፈሪ ሜዳ አይነሱም ለፈሪ ምድር አይበቃውም ለፈሪ ይበቃል ፍርፋሪ ለፈሪ ስጠው ፍርፋሪ ለፋሲካ የተዳረች ሁል ጊዜ የፋሲካ ይመስላታል ለፍቅር ብተኛት ለጠብ አረገዘች ለፍቅር የለውም ድውር ለፍየል ቆላ ለሙክት ባቄላ ለፍየል ህመም በሬ ማረድ ለፍየል ስም አውጣ ቢለው ሞት አይደርስ አለው ሊበሉዋት ያሰብዋትን አሞራ ይሏታል ጂግራ ሊወጋ የመጣ ጌታዬ ቢሉት አይመለስም ሊያልፍ ውሀ አደረገኝ ድሀ ሊያስቡት አይገድም ሊጣላ የመጣ ሰብብ አያጣም ላህያ ፈስ አፍንጫ አይዙለትም ላህያ ማር አይጥማት ላህያ ያልከበደው ለመጫኛ ከበደው ላለው ቅንጭብ ያረግዳል ላለው ይጨመርለታል ላለፈ አይጸጸቱም ለሚመጣው አይበለጡም ላለፈው አይጸጸቱም ለሚመጣው አይበለጡም ላለፈው ክረምት ቤት አይሰራለትም ላለፈው ክረምት ውሀ ማቆር አይቻልም ላለፈው ጸሎት ከንቱ ጩኸት ላሊበላ ሄደሽ ከህንጻው ብትሰፍሪ አይገኝም ጽድቅ አለ ባህሪ ላሊበላ አደራውን አይበላ ላሊበላ የቃሉን አይበላ ላሊበላን ካላጠገቡት ይጮሀል ሎሌም ካልሰጡት ይከዳል ላላየ ልጅ ዳቦ ፍሪዳው ላላየው የሚያስገርም ለሰማው የሚያስደንቅ ላላዩ ልጅ ዳቦ ፍሪዳው ላላወቀው ፎገራ ዱር ነው ላመት ልብስ ለእለት ጉርስ ላሜ ቦራ የልጆቼን ነገር አደራ ላም ሲበዘበዝ ጭራዋን ያዝ ላም ቀንዷ አይከብዳትም ላም በረቱን የሰው ልጅ አባቱን አይረሳም ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ላም አለኝ በሰማይ ወተትዋንም አላይ ላም አለኝ በሰማይ ገመድ እፈልጋለሁ ላም እሳት ወለደች እንዳትልሰው ፈጃት እንዳትተወውም ልጅ ሆነባት ላም ከወንዝ ልጅ ከቦዝ ላንተ መምከር ጥቁር ድንጋይ ላይ ውሀ ማፍሰስ ነው ላንቺ ቁምነገርሽ በሶብላ ወጥሽ ላንቺ ብርቅሽ በሶቢላ ወጥሽ ላያዘልቅ ጸሎት ለቅስፈት ላይቀርልኝ እዳ በጊዜ ልሰናዳ ሌባ ላመሉ ቅድመ እውቅና አገኘ ሌባ ላመሉ ንግድ ይላል ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል ሌባ እናት ልጇን አታምንም ሌባን ሌባ ቢሰርቀው እንዴት ይደንቀው ልባም ሴት ለባልዋ ዘውድ ናት ልብስህን በውሀ ገንዘብህን በድሀ ልብ ካላየ አይን አያይም ልብ ካላየ አይን አይፈርድም ልትደርቅ የደረሰች ምንጭ ጭልጭል ትላለች ልትሰራ ሂዳ ተላጭታ መጣች ልጅም ከሆነ ይገፋል ድንችም ከሆነ ይጠፋል ልጅ ለናቷ ምጥ አስተማረች ልጅ ምን ቢሮጥ አባቱን አይቀድምም ልጅ ሳለህ አጊጥ ሞል ሳይዘጋ ሸምት ልጅ ቢያኮርፍ ቁርሱ እራት ይሆናል ልጅና እሳት ባለቤቱ ያጠፋዋል ልጅን አሳዳጊ እሳትን ውሀ ያጠፋዋል ልጅና ወረቀት የያዘውን አይለቅም ልጅና ጦጣ ውሀ ይጠጣ ልጅ ያቦካው ለእራት አይሆንም ልጅ ይወለዳል ከቦዝ ላም ይገዛል ከወንዝ ልጅ ደረሰ ቤት ፈረሰ ልግመኛ ባሪያ መጇን ትደብቃለች ልግመኛ አጋዥ ብታገኝ መጅ ደበቀች ልግመኛን መምከር ውሀ በወንፊት ማኖር ልፋት ቢያምርህ መሬት ግዛ ችግር ቢያምርህ ልጅ አብዛ ልፋ ያለው ሊስትሮ እግር ስር ይውላል ልፋ ያለው ምረጡኝ አለ ልፋ ያለው በህልሙ ሲሸከም ያድራል ልፋ ያለው አንድ እንጨት ያስራል ልፋ ያለው በሬ ቆዳው ለከበሮ ልፋ ያለው ቢን ላደንን ይፈልጋል ልፋ ያለው አንድ እንጨት ያስራል ሎሌ ለስህተት ጌታ ለምህረት ሎሌ ሲከብር ጌታውን ይከሳል ሙክት ሲሰባ ሾተሉን ይልሳል ሎሌ ያገለገለውን ይቆጥራል ጌታ ያስቀየመውን ያስባል ሎሌና አሞሌ ካዘዙት ይውላል ሎሚ ካልመጠጡት እምቧይ ነው ሎሚ ካልመጠጡት እምቧይ ዳቦ ካልገመጡት ድንጋይ ሎሚና ትርንጎ ሞልቶልህ ባገር እንቧይ ታሸታለህ የድሀ ነገር ሎሚና ትርንጎ ሞልቶ ባገር እንቧይ ያሸታል አወይ የድሀ ነገር ሎሚ ቢያብብ ቢኖርና መልካም ሽታ ቢሰጥ መኮምጠጡን አይተውም መሄድ በጋ ነው መቀመጥ ክረምት ነው መሄጃ የሌለው መውጫውን ያበስራል መልከ ጥፉ በስም ይደግፉ መልከ ጥፏ ቆንጆዋን አስናቀች መልካም ባል መጥፎ ሴት ይገራል መልካም ሴት ለባሏ ዘውድ ናት መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላል መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይቆማል መልካም አባት ለልጆቹ እጁን ኪሱ ይከታል መልካም ባል መጥፎ ሴት ይገራል መልኳ ባያምር አመሏ ይመር መልክ ታጥቦ አይጠጣ ወይ አይበላ መልክ ስጠኝ እንጂ ሙያ ከጎረቤቴ እማራለሁ መመራመር ያገባል ከባህር መሞት የፈለገ ግልገል ቀበሮ ቤት ሄዶ ይጨፍራል መራጭ ይወድቃል ከምራጭ መቀመጥ በአልጋ ታላቅ ደጋ መቅረቧን ሳታውቅ እጇን ታጠበች መብላቷን ሳታውቅ እጇን ታጠበች መተው ነገሬን ከተተው መቼ መጣሽ ሙሽራ መቸ ቆረጠምሽ ሽንብራ መካር የሌለው ንጉስ አለ አንድ አመት አይነግስ መንገድ ካገር ልጅ ምክር ከጨዋ ልጅ መወለድ ቋንቋ ነው ሚስቱ ክፉ ባቄላ እራቱ ብሳና እንጨቱ ሀዘን ነው እቤቱ ሚስቱ ደግ ስንዴ እራቱ ወይራ እንጨቱ ደስታ ነው እቤቱ ሚስቱን ጠልቶ ካማቱ ልጁን ከሶ ካባቱ ሚስቱን ገድሎ አማቱ ቤት ተሽሽገ ሚስት ባታብል ባሏን ትወልዳለች ሚስት ከፈቷት ባዳ ማሽላ ከተቆረጠ አገዳ ሚስትህ አመዳም ጎራዴህ ጎመዳም ሚስትህ አረገዘች ወይ ቢለው ማንን ወንድ ብላ አለው ሚስትህን ስደድ በሬህን እረድ ይላል የባለጌ ዘመድ ሚስትና ዳዊት ከብብት ሚስት ፈትቶ ካማት መቀለብ በእንፉቅቅ መሄድ ሙቅ ውሀና የሰው ገንዘብ አይጠቅምም ሚስጥርህን ለባእድ ለምን አዋየኸው ወንፊት ወሀ ይዞ የት ሲደርስ አየኸው ማሞ ሌላ መታወቂያው ሌላ ማር በበላሁበት በጣፈጠው አፌ ጎመን ጎረስኩበት አይ አለማረፌ ማሽላ ሲያር ይስቃል ማሽላ እየፈካ ያራል?? ማቅ ይሞቃል ጋቢ ይደምቃል ገቢውን ባለቤት ያውቃል??? ማን ሙሽራ ሊልሽ ትኳያለሽ ማን ያውራ የነበረ ማን ያርዳ የቀበረ ማእድ ጠፋና አንድ ላይ በላን ማግባቱ ቀርቶብኝ በታጨሁ ማጣት ከሰማይ ይርቃል ምላጭ ቢያብጥ በምን ይበጡ ውሀ ቢያንቅ በምን ይውጡ ምን ያመጣ ድሀ ምን ያገሳ ውሀ ምን ቢያርሱ እንደጎመን አይጎርሱ ምንም ቢጠም መንገድ ምንም ቢከፋ ዘመድ ምን ቢፋቀሩ አብረው አይቀበሩ ምከረው ምከረው እንቢ ካለ መከራ ይምከረው ሞት በጥር በነሀሴ መቃብር ሞት ቢዘገይ የቀረ ይመስላል ሞት የሰጠው ቀባሪ አያሳጣውም ሞኝ ሲስቁበት የሳቁለት ይመስለዋል ሞኝ እከኩን እያየች ስትስቅበት ወደደችኝ ብሎ ይፈነድቃል ሞኝና ወረቀት ሊደራደሩ ነው ሞኝና ወረቅት የያዘውን አይለቅም ሞኝ ውሀ ሲወስደው ይስቃል ሞኝ ዘመድ ከልጅህ እኩል አድርገኝ ይላል ሬሳ በምኑ ይከበራል በዝምታው ራስ ሳይጠና ጉተና ራስ ተላጭቶ ወለባ ልባልባ ታጥቆ አዛባ ሰለሞን ሳባን ውሀ ባያስጠማት ኖሮ የሱ ጥም ባልበረደ ነበር ሰውን ፈላጊ በምርጫ ይሽነፋል ሰማይ አትረስ ንጉስ አትክሰስ ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ ሰባት አመት ባይማሩ ሰባ አመት ይደንቁሩ ሰነፍ ሴት ያገባ በሬው በሰኔ ገደል የገባ ሰነፍ በዓል ያበዛል ሰነፍ ቢመክሩት ውሀ ቢወቅጡት ሰነፍ ገበሬ በሰኔ ይሞታል ሰነፍ ገበሬ ክረምት በጋው በጋው ክረምቱ ሰኔ መቃጠሪያ ህዳር መገናኛ ሰኔ ሰላሳ የለውም ካሳ ሰኔና ሰኞ ሰኔን በዘራዘር ሃምሌን በጎመን ዘር ሰካራም ቤት አይሰራም ሰካራም ዋስ አያጣም ሰው መሳይ በሸንጎ ሰው በዋለበት ውሀ በወረደበት ሰው ቢማር ቄስ እንጂ መላክ አይሆንም ሰው ባለው ይሰለፋል ሰውን ማመን ቀብድ ተቀብሎ ነው ሰውን ሰው ናቀው የራሱን ሳያውቀው ሰውን ሰው ያሰኘው እቁብ ነው ሰውን ሲወዱ ከነንፍጡ እና ልጋጉ ሰውን ሲያማ ለእኔ ብለህ ስማ ሰው አለብልሀቱ ገደል መግባቱ አለጉልበቱ ውሀ መግባቱ ሰው አለወንዙ ብዙ ነው መዘዙ ሰው እንደ እውቀቱ ነው ሰው ከሞተ የለ ንስሀ ከፈሰሰ አይታፈስ ውሀ ሰውየው ውሀ ሲወስደው እኔም ወደ ቆላ እወርዳለሁ ብዬ ነበር አለ ሰው ያመነ ውሀ የዘገነ ሰው ያስገድላል አባይ ውሀ ያስጮሀል ድንጋይ ሰው ያለስራው የተሰረቀ አህያ ይነዳል ሰው ጥራ ቢሉት መራራን ጠራት ሰው ጥራ ቢሉት እራሱ መጣ ሰዶ ማሳደድ ቢሻህ ዶሮህን ለቆቅ ለውጥ ሰዶ ማሳደድ ካማረህ ዶሮህን በቆቅ ለውጥ ሲሉ ስምታ ዶሮ ሞተች ዋና ገብታ ሲመክሩት ያልሰማ ሲያጮሉት ይሰማ ሲመች ያማት ተዝካር ይወጣል ሳይመች ያባት ይቀራል ሲሞቱ ብታይ አንቀላፋች ሲሮጡ የታጠቁት ሲሮጡ ይፈታል ሲሮጡ የፈቱት ሲቀመጡ ለማስተካከል ቀላል ነው ሲሮጥ የመጣን አህያ አጥብቀህ ጫነው ሲሰርቀኝ ያየሁትን ቢጨምርልኝ አላምነውም ሲስሟት ትታ ሲስቧት ሲስሟት እንቢ ብላ ሲጎትቷት ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል ሲበሉ አድርሰኝ ሲጣሉ አርቀኝ ሲበሉ አድርሱኝ ሲጣሉ መልሱኝ ሲቃ የቀስቀስው ነቅቶ አይተኛም ሲታጠቡ እስከ ክንድ ሲታረቁ ከሆድ ሲቸኩሉ የታጠቁት ለወሲብ አይመችም ሲቸግር ጤፍ ብድር ሲያውቀኝ ናቀኝ ሲያዩት ያላማረ ሲበሉት ያቅራል ሲያደርጉ አይታ ዶሮም ጡት መያዣ ገዛች ሲጠሩት ወዴት ሲልኩት አቤት ሲጠባ ያደገ ጥጃ ቢይዙት ያጓራል ሲገደገድ ያልበጀው ሲወቀር እሳት ፈጀው ሳል ይዞ ስርቆት ቂም ይዞ ጸሎት ሳትወልድ ብላ ሳያሽ የበላ ዝንጀሮ ሲስል ያድራል ሳያውቁ የቆረጡት አበባ የፈለጉት ቀን ይደርቃል ሳያጣሩ ወሬ ሳይገሉ ጎፈሬ ሳይርቅ በቅርቡ ሳይደርቅ በቅርቡ ሳይሰሙ ወሬ ሳይገሉ ጎፈሬ ሳይቃጠል በቅጠል ሳይተርፋት አበድራ ሳትቀበል ሞተች ሳይቸግር ጤፍ ብድር ሳይቸግር ጤፍ ብድር መከበር በከንፈር ሳይቸግር ጤፍ ብድር በስተርጅና ሙሽርና ሳይከካ ተቦካ ሳይደግስ አይጣላም ሳይጠሩት አቤት የሰይጣን ጎረቤት ሳይጠሩት ወይ ባይ ሳይሰጡት ተቀባይ ሴቱ ሲበዛ ጎመን ጠነዛ ሴትና ዶሮ ዱር ከሄዱ ቤታቸውን ይክዳሉ ሴት ከወንድ እህል ከሆድ ሴት ለቤት ወፍጮ ለዱቄት ሴትና መሬት የማይችሉት የለም ሴት ማገዶ ሲቸግራት ምሰሶ ትነቅላለች ሴት ሲበዛ ልማት ይፋጠናል ሴት ሲበዛ ወንዶች ይፈራሉ ሴት በማጀት ወንድ በችሎት ሴት በጳጳስ ኳደሬ በንጉስ ሴት ብታውቅ በወንድ ያልቅ ሴት ሲያፏጩላት ያረሱላት ይመስላታል ሴት ታውቅ በወንድ ያልቅ ሴት አማት የመረዘው ኮሶ ያነዘዘው ሴት አግብተው ሴት ቢወልዱ የት አለ ንግዱ ሴት ከወንድ እህል ከሆድ ሴት ከጠላች በቅሎ ከበላች አመል አወጣች ሴት ካላበለች ባልዋን ትወልዳለች ሴት ካልወለደች ቋንጣ አትጠብስም ሴት ካልዋሸች ባልዋን ትወዳለች ሴትና መሬት የማይችሉት የለም ሴት የወደደ ጉም የዘገነ ሴት ያመጣው ጠብ አይበርድም ሴት ይወዷል ማጀት ያንጎዳጉዷል ሴትና ቄስ ቀስ ሴትና በቅሎ እንደገሪዋ ነው ሴትና አህያ በዱላ ሴትና አህያ ዱላ ይወዳል ሴትና ድመት ወደ ሞቀበት ሴትና ዶሮ ሳይጣላ አይውልም ሴትና ድስት ወደ ማጀት ሴትና ዶሮ ሳያብድ አይውልም ሴትና ፈረስ እንደኩሬ ውሀ እያደር ማነስ ሴትና ፈረስ የስጡትን ይቀምስ ሴትን ያመነ ጉም የዘገነ ሴት የላከው ምልክቱን አይረሳም ሴት የላከው ሞት አስፈራራው ሴት የላከው ሞት አይፈራም ሴት የላከው በር አያንኳኳም ሴት የላከው አልቃይዳን አይፈራም ሴት የላከው ጅብ አይፈራም ሴት የላከው ፓርላማ ይገባል ሴትየዋ እንደፈራሁት ተቀደደብኝ አለች ስለ ጨሰ አይነድም ስለዳመነ አይዘንብም ስልቻ ቀልቀሎ ቀልቀሎም ስልቻ ስምህ ማነው ላገር አይመች ማን አወጣልህ ጎረቤቶች ስምሽ ማነው ሲሏት ቂጤ ትልቅ ነው አለች ስምን መላክ ያወጣዋል ስም ከመቃብር በላይ ይቆማል ስም ያለው ሞኝ ነው ስም ይወጣል ከቤት ይሄዳል ጎረቤት ስም ይወጣል ከቤት ይከተላል ጎረቤት ስራ ለሰሪው ምርጫ ለመራጭ ስራ ለሰሪው እሾህ ላጣሪው ስራ ከመፍታት ምርጫ መወዳደር ስራ ከምፈታ ልጄን ላፋታ ስራ ያጣ መለኩሴ አደገኛ ቦዘኔ ተባለ ስራ ያጣ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል ስራ ያጣ መነኩሴ “አደገኛ ቦዘኔ” ተብሎ ታሰረ ስራ ያጣ መነኩሴ የምርጫ ቅስቀሳ ጀመረ ስራ ያጣ ቄስ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል ስብ ሊያርዱ ጉፋያ ይነዱ ስትወልድ የምትበላውን በርግዝናዋ ጨረስችው ስትግደረደሪ ጾምሽን እንዳታድሪ ስደትና አግዳሚ ሁሉንም እኩል ያረጋል ስጋ ቁጠር ቢሉት ጣፊያ አንድ አለ ስጋው ያሳማ እንኳን ለበላው ለሰማው ገማ ስጋው ያሳማ ከበላው የሰማው ገማ ሶስቴ ከመፍሳት አንዴ መቅዘን ሸማ ለብሶ ስልቻ በቅሎ ጭኖ ለብቻ ሸማ ማዋስ ለባላገር በቅሎ ማዋስ ለወታደር ሸማ በውሀ ሰው በንስሀ ሸማን በውሀ ሰውነትን በንስሀ ሸማ በየፈርጁ ይለበሳል ሸማና ምስጥ ወደ ውስጥ ሸማኔ በመኑ ጠይብ በከሰሉ ሸማኔ በድሩ ጠይብ በመንደሩ ሸማኔ ድውሩን ባለስልጣን ክብሩን ሸማን ጠምዞ ያሰጧል እህልን አላምጦ ይበሏል ሸምበቆ በመርዘሙ አይሆንም ምሰሶ ሸምበቆ በመርዘሙ ምሰሶ አይሆንም ሸርሙጣ ስታረጅ አቃጣሪ ትሆናለች ሸርሙጣን የወደደ ልብሱን ጥሎ አበደ ሸርሙጣን የወደደ ልብሱን ጥሎ ያበደ ሸኚና ጥላ ቤት አይገባም ሸኚ ቤት አያደርስም ሸኝ ቤት አይገባም ሸክላ ቢጥሉት ገለባ ሹመት ላወቀው ይከብደዋል ላላወቀው ያሳብደዋል ሹመት ሲገኝ ዘመድ አይገድም ሹመት ሺህ ሞት ሹመት በተርታ ስጋ በገበታ ሹመት የለመደ ወንዝ ዳር ይወርዳል ሹመትና ቁመት ከልኩ አያልፍም ሹመትና ቁመት አይገኝም በምኞት ሹም ለመነ አዘዘ ሹም ለሹም ያወርሳል ጉም ተራራ ያለብሳል ሹም ለሹም ይጎራረሳል ድሀ ለድሀ ይለቃቀሳል ሹም መክሰስ ወጀድ ማረስ አይቸግርም ሹም ሲቆጣ ማር ይዞ እደጁ ደስ ሲለው ማር ይዞ እደጁ ሹም ቢሞት ሀምሳ የሹም ልጅ ቢሞት መቶ ሀምሳ ሹም ቢሞት ቀባሪው ሀምሳ የሹም ልጅ ቢሞት መቶ ሀምሳ ሹም ያዛል ቄስ ይናዝዛል ሹምና ማር እያደር ይከብዳል ሹምና የጋማ ከብት በጊዜ ይከተት ሹምና ጥጥ እያደር ይከብዳል ሹምና ጥጥ እያደር ይከዳል ሹሩባ ትሰራ ሄዳ ጠጉሩዋን ተላጭታ መጣች ሹክሹክታ የጠብ ወለምታ ሺ መት ሺ ሞት ሺም ታለበ አንድ ያው በገሌ ሺ በመከረ አንድ በወረወረ ሺ በመከር አንድ በወረወር ሺ አውል ሲሞት ሺህ ይሙት ሺ አውል ከሚሞት ሺ ይሙት ሺ አውል ኪሞት ሺ ይሙት ሺ ይሙቱ ሺ አውል አይሙት ሺ ዝንብ መሶብ አይከፍትም ሺህ ቢታለብ አንድ በገሌ አለች ድመት ሺ ቢታለቡ ከገሌ አላልፍም አለች ድመት ሺ ቢያጩሽ አንድ ያገባሽ ሺ ያጭሽ አንድ ያገባሽ ሻማ ራሱ ነዶ ራሱ ብርሀን ይሰጣል ሻሽ ይደምቃል ማቅ ይሞቃል የሚበጀውን ባለቤቱ ያውቃል ሻጭ ገዥ ሆኖ ይገምታል ሽልም እንደሆን ይገፋል ቂጥም እንደሆን ይጠፋል ሽል ከሆነ ይገፋል ቂጣም ከሆነ ይጠፋል ሽል እንደሆን ይገፋል ቂጣም እንደሆን ይጠፋል ሽመልና ዘንግ ቂልና በግ ሽማግሌ ሳለ ምክር አይጠፋም ጎልማሳ ሳለ ላም አይነዳም ሽማግሌ በምክሩ አርበኛ በሰናድሩ ሽማግሌ ካለበት ነገር አይናቅበት ሽማግሌ ካለበት ነገር አይሰረቅ ጎበዝ ካለበት በትር አይነጠቅ ሽማግሌ ካልሞተ ስንዴ ካልመረተ ሽማግሌ ካልሞተ ስንዴ ካልሸተ ሽማግሌ ይገላግላል የተጠቃ አቤት ይላል ሽማግሌና ስልቻ ሳይሞሉ አይቆሙም ሽማግሌና ጅብ በላላባት ይገባል ሽማግሌን ከምክር ከመለየት ከምግብ መለየት ሽሮን ሲሸውዷት ፕሮቲን ነሽ አሏት ሽሽት ከኡኡታ በፊት ሽበት ምን ታረግ መጣህ ቢሉት እኖር ብዬ አለ ሽበት እኖር ብዬ መጥቻለሁ አለ ሽታና ግማት ላልሰማ ማውራት ሽንብራ መኖር በመከራ ሽንኩርት አንድም በሉት ገማ ደገሙትም ገማ ሽንኩርት የባህሪውን ይሸታል ሾላ በድፍን ሾተልን ወደ ሰገባህ ቁጣህን ወደ ትእግስት ሾተልን ወደ አራዊት ቁጣህን ወደ ትእግስት ሾተልን ወደ አፎት ቁጣን ወደ ትእግስት ሽሮ ቢደነፋ እንጀራ እስኪቀርብ ነው ቀለም ሲበጠበጥ ብርእ ሲቀረጥ ቀለም በቀንድ ውስጥ ጨለማ ነው ሲፃፍ ግን ብርሃን ነው ቀለም ሲበጠበጥ ብርእ ቅረጹልኝ ቀለበት ለቆማጣ ሚዶ ለመላጣ ቀሊል አማት ሲሶ በትር አላት ቀላጅ የሰይጣን ወዳጅ ቀላዋጭ ወጥ ያውቃል ቀልብ የሌለው ውሻ ጠዲቅ አምጡልኝ ይላል ቀልድና ቅዘን ቤት ያጠፋል ቀልደኛ አልቅሶ ካልተናገረ የሚያምነው የለም ቀልደኛ ገበሬ ሲያስቀን አደረ ቀልደኛ ገበሬ ናይት ክለብ ከፈተ ቀልደኛ ጎረምሳ እያራ ያፏጫል ቀልድና ቅዘን ቤት ያበላሻል ቀሙን ላይቀር ከነጫማቸው ቀማኛና ሽፍታ ጭለማና ማታ ቀርቀሬ ወርጄ ማር ስልስ ማር ልከፍል ቀስ በመቀስ አንቁላል በአግሩይሂዳል ቀስ እንዳይደፈረስ ቀስ እንዳይፈስ ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል ቀስ በቀስ አባይም ዝናብ ይሆናል ቀበሮ ናት የገጠሩዋ ሚዳቋ ናት የሰፈሩዋ ቀበሮ የበሬ ቆለጥ ይወድቅልኛል ብላ ስትከተል ዋለች ቀበቶ ለማፈኛ ሰንሰለት ለማቆራኛ ቀበኛ ማሰሪያውን በልቶ ያሳጥራል ቀበኛ ከብት ዋጋውን ያደርስ ቀባሪ በፈጣሪ ቀብረው ሲመለሱ እግዜር ይማርዎ ቀብሮ የሚመለስ የሚመለስ አይመስለውም ቀኑ የጨለመበት መንገዱ ዘንግ ነው ቀና ሲታጣ ይመለመላል ጎባጣ ቀና ቢታጣ ይመለመላል ጎባጣ ቀናውን ብነግራት ውልግድግዱን አለች ቀን ስው መስሎ ማታ ጅራት አብቅሎ ቀን ሲከፋ በግ ይነክሳል ቀን ሲጥለው ሁሉ ይጠላው ቀን ሲገለበጥ ውሀ ወደ ላይ ይፈሳል ቀን ሲደርስ አምባ ይፈርስ ቀን ሳይቆጥሩ ውሻ ሳይጠሩ ደረሰ በእግሩ ቀንበር ታርቆ ጣውንት ታርቆ ምን ይሆናል ቀንበር ታንቆ ጣውንት ታርቆ ምን ይሆናል ቀን በበቅሎ ማታ በቆሎ ቀን በቅሎ ማታ ቆሎ ቀን ቢረዝም ልብ ያደክም ቀን ቢረዝም ልብ ይደክም ቀን ቢቆጥሩ ውሻ ቢጠሩ ደረሰ በእግሩ ቀን ቢቆጥሩ ውሻ ቢጠሩ ይደርሳል በእግሩ ቀን ባጀብ ሌት በዘብ ቀን አይጥለው የቀለም ሰረገላ አያሰናክለው ቀን አይጥለው ጠጅ አያስክረው ቀን አይጥለው ጠጅ አያሰክረው የለም ቀን እስኪወጣ ያባቴ ገበሬ ያግባኝ ቀን እስኪያልፍልሽ ያባትሽ ሎሌ ያግባሽ ቀን እስኪያልፍ ያለፋል ቀን እስኪያልፍ ያባቴ ባሪያ ያግባኝ ቀን እስኪያልፍ ያባቴ ባሪያ ይግዛኝ ቀን እንደተራዳ ሌት እንደ ግርግዳ ቀን ከህዝብ ሌት ከጅብ ቀን ከጣለው ሁሉ ይጥለው ቀን ካልለቀሙ ሌት አይቅሙ ቀን ካለቀሙ ሌት አይቅሙ ቀን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል ቀን የጎደለበት ጠገራ አይጥ ይበላዋል ቀን ይነዳ እንደ ፍሪዳ ቀንና ጨርቅ እንደምንም ያልቅ ቀንና ጨርቅ ያልቃል ብልህ ያውቃል ቀንዳምን በሬ ቀንድ ቀንዱን ቀንዱ ሰማይ ጠቀስ ጭራው ምድር አበስ ቀንድ ካላት ላም ጎዳ ትከፋለች ቀንድና ጅራት ለዋንጫ አለፉ ቀንድ እገባበት ጅራት አይቀርም ቀንድ ውስጥ ገብቶ ጅራት አይቀርም ቀኝም ሰገሩ ግራም ሰገሩ መገናኛው ኮሩ ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ ቀድሞ ነበር እንጂ ተራምዶ ማለፍ አሁን ምን ይሆናል ተይዞ መለፍለፍ ቀይ ምላሱ ጥቁር እራሱ ቀይ ሰው መልክ አይፈጅም ቀይ እንደበርበሬ ጥሩ እንደ ብርሌ ቀዳዳ ያፈሳል ግቢ ያፈርሳል ቀድሞ ሰኞን አለመሆን ነው ቀድሞ የሸተውን ወፍ ይበላዋል ቀድሞ የሚናገረውን ሰው ይጠላዋል ቀድሞ የሸተውን ወፍ ይበላዋል ቀድሞ የተናገረውን ሰው ይጠላዋል ቀዶ ያለበሰ ቆርሶ ያጎረሰ ቀጥኜ ቢያየኝ ጅማት ለመነኝ ቀጥኜ ቢያዩኝ ጅማት ለመኑኝ ቀጥኜ ቢያዩኝ ሞዴል ነሽ አሉኝ ቁልቢጥ የላት ቁና አማራት ቁልቢጥ የላት ድርጎ አማራት ቁመህ ተከራከር ዙረህ ተመካከር ቁመህ ተናገር ዙረህ ተመካከር ቁመቷ ቢያጥር እንደ ድምብላል ውዷ ክፉ ነው ይደበልላል ቁም እንደአላማ ቁረጥ እንደጫማ ቁም እንዳላማ ጥልቅ እንደጫማ ቁም ነገረኛ መምሰል የተለመደ አመል ቁም ነገር ይዞ ተረት ቂም ይዞ ጸሎት ቁራ ሲነጣ አህያ ቀንድ ያወጣ ቁራ ስሙን የጠራ ቁርበት ምን ያንቋቋሀል ቢሉት ባያድለኝ ነው እንጂ የነጋሪት ወንድም ነበርኩ አለ ቁርበት ምን ያንጓጓሀል ቢሉት ባያድለኝ ነው እንጂ የነጋሪት ወንድም ነበርኩ አለ ቁርጥማት ቢያብር አልጋ ላይ ያማቅቃል ቁርጥ ያጠግባል ተስፋ ያታልላል ቁቅም ከፈስ ተቆጠረች ቁና ለመስፈሪያ ብርብራ ለማስከሪያ ቁንጥጫ ይሻላል ከግልምጫ ቁንጫ ለትልቅ ሰው ይበረታል ይባላል ቁንጫ መሄድ ሳትማር መዝለል ትማራለች ቁንጫ ሞኝ ናት ቀን ትበራለች ተለቃቅማ ታልቃለች ቁንጫ ውሀ ወረጅ ቢሏት ስፈናጠር የሰው ዶጮ እሰብር አለች ቁጥቋጦም ሲያድግ ዛፍ ይሆናል ቁጥቋጦ ሲያድግ ዛፍ ይሆናል ቁጥቋጦ ያለዛፍ አይሆንም ቁጩና ብስጩ አልማችሁ ፍጩ ቁጭትና መረቅ ለጊዜው ይጣፍጣል ቁጭትና መጠጥ ለጊዜው ይጣፍጥ ቁፍ ቁፍ አሰኘሽ እንደቄብ ዶሮ ለመከራ ላሳርሽ ኖሮ ቂል ሲረግሙት የመረቁት ይመስለዋል ቂል አይሙት እንዲያጫውት ቂልን ለብቻው ስደበው ራሱን ባደባባይ እንዲሰደብ ቂልን አንድ ጊዜ ስደበው ሲሰደብ ይኖራል ቂልን ድንጋይ ተማትቶ ጌታና ሎሌ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ ቂል ከጠገበበት አይወጣም ቂል ያገኘው ፈሊጥ ውሻ የደፋው ሊጥ ቂምህን አትርሳ የወደቀን አንሳ ቂም ይዞ ጸሎት ሳል ይዞ ስርቆት ቂም ይዞ ጸሎት ጭድ አዝሎ ወዘት ቂጡን የተወጋ ውሻ እንደልቡ አይጮህም ቂጡ የቆሰለ ውሻ እንደልቡ አይጮህም ቂጥ ቢወድል ፈስ አያድን ቂጥ ቢያብጥ ልብ አይሆንም ቂጥኛም ከውርዴ ይማከራል ቂጥኛም ከውርዴ ይውላል ቂጥ ገልቦ ክንብንብ ቂም ቂም ያሰኘሽ እንደዶሮ ለካስ ለመከራሽ ላሳርሽ ኖሮ ቂፍ ቂፍ ያሰኘሽ እንደ ቄብ ዶሮ ለመከራሽ ላሳርሽ ኖሮ ቃልህ ሳይዘጋ እግርህ ሳይዘረጋ ቄሱም ዝም መጽሀፉም ዝም ቄስ ለኑዛዜ ፍቅር ለሚዜ ቄስ ምን ይሻል ጠላ ነገር ምን ይሻል ችላ ቄስ ኤርክሶን መምህሩ እናት አያስቀብሩ ቄስ እበር አረመኔ ከማህበር ቄስ ካናዘዘው እድሜ ያናዘዘው ቄስ ካፈረሰ ዲያቆን ከረከሰ ቄስና ንብ እያዩ እሳት ይገባሉ ቄስና ንብ እያየ እሳት ይገባል ቄስ ያዘዘህን አድርግ እንጂ ቄስ ያደረገውን አታድርግ ቅል ባገሩ ድንጋይ ይሰብራል ቅል ባገሩ ደንጊያን ይሰብራል ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ሎሌና ጌታ ተሟግቶ ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ሎሌና ጌታ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ጌታና ሎሌ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ ቅልውጥ አሳስቦ ይጥላል ዘመቻ ቅምሙ የበዛበት ወጥ አይፋጅ አይኮመጥጥ ቅማል እንኳን ካቅሟ ጥብጣብ ታስፈታለች ቅማል ውሀ ውረጅ ቢሏት ስንዳሰስ ለመቼ ልደርስ ቁንጫ ውሀ ውረጅ ቢሏት ስፈናጠር የሰው ዶጮ እሰብር አሉ ቅማል በጥፍር ቢድጧት ራስ ደህና አለች ቅማል ከአካላት ምስጢር ከቤት ቋንጣና ባለሟል ሳያር አይቀርም ቅዝምዝም ወዲያ ፍየል ወዲህ ቅርብ ያለ ጠበል ልጥ ይነከርበታል ቅርናታም ለቅርናታም ሰንቡሌ ሰንቡሌ ይባባላል ቅርንጫፉ እንደዛፉ ቅቤ መዛኝ ድርቅ ያወራል ቅቤ ሲለግም ወስፌ አይበሳውም ቅቤ ተነጥሮ ለመብላት ያባት የናት ቅቤና ቅልጥም ወዴት ግጥምጥም ቅቤ ይፍሰስ ከገንፎ አይተርፍ ቅቤ ይፍሰስ ከገንፎ አይለፍ ቅብጥና ቅልጥ አንድ ላይ ሲሄዱ ቅልጥ ብላ ቀረች ሶራስ ክመንገዱ ቅል በአገሩ ድንጋይ ይሰብራል ቅናት ያደርሳል ከሞት ቅናት ጥናት አያገናኝ ካባት ከናት ቅናት ጥናት አይገኝም ከናት ካባት ቅና ያለው በአባቱ ከረባት ይቀናል ቅና ያለው በናቱ ብልት ይቀናል ቅን በቅን ከማገልገል ፊት ለፊት ማውደልደል ቅንቡርስ የት ትሄዳለህ መተማ ትደርሳለህ ልብማ ቅንነት ለነፍስ መድሀኒት ቅንድብ ለአይን ጥቅሻ አስተማረች ቅዝምዝም ሲወረወር ጎንበስ ብለህ አሳልፈው ቅዠት ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም ቆላና ደጋ እመቤትና አልጋ ቆሎ ለዘር እንዶድ ለድግር አይሆንም ቆሎን ቢቆረጥሙት እንጂ ቢያሹት አያልቅም ቆመው የሰቀሉትን ቁጭ ብለው ለማውረድ ይቸግራል ቆማጣ ቤት አንድ ጣት ብርቅ ናት ቆማጣ ብለው ያው ቁምጥና ነው ሌላ ምን ይመጣል አለ ቆማጣን ቆማጣ ካላሉት ገብቶ ይፈተፍታል ቆሩ መቀበሪያው ያው ፈሩ ቆሩ በማን ምድር ትለፋ ቆርሶ ያላጎረሱትን ቀዶ ያላለበሱትን ብላቴና ማዘዝ አይገባም ቆቅ ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ቆንጆና እሸት አይታለፍም ቆዳ ማንጓጓቱን ስሱ መጓጓቱን ቆዳ ማንጓጓቱን ስሱ መጓጓቱን አይተውም ቆዳ ሲወደድ በሬህን እረድ ቆጥሮ የማይሰጥ ሌባ ቆጥሮ የማይቀበል ሌባ
12691
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%8A%AD%E1%88%B1%E1%88%9D%20%E1%88%90%E1%8B%8D%E1%88%8D%E1%89%B5
የአክሱም ሐውልት
የአክሱም ሃውልት (እንግሊዝኛ: ) ወይም እየተባለ በተለምዶ የሚጠራው በኢትዮጲያ በአክሱም ከተማ የሚገኝ የአለማችን ረጅሙ ትክል ድንጋይ ሃውልት ነው። ይህ ሀውልት 1700 ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን የ24 ሜትር (78 ጫማ) ርዝመት አለው። 160 ቶን የሚመዝነው ይህ ግዙፍ ድንጋይ መሠረቱ አከባቢ ሁለት የሀሠት በር መሣይ ፍልፍሎች አሉት። የዚህ ሀውልት ጌጥ ይህ ብቻም አይደለም በያንዳንዱ ጎን የመስኮት ቅርጽ የያዙ ፍልፍሎች ሲኖሩት በመጨረሻው ጫፍ ላይ ደግሞ በብረት ፍሬም የታገዘ የግማሽ ክብ ነው::በወቅቱ የሚመለክ ጣዖት ነበር። በአክሱም ዘመነ መንግስት እንዲገነባ የተደረገው ይህ ሀውልት ወይም በእንግሊዝኛው "" የሚባለው በአክሱም ከተማ ከሌሎች መሠል ሀውልቶች ጋር ኢንዲቆም የተደረገው በ4ኛው ምዕተ አመት አካባቢ ሲሆን። ይህም የጥንታዊ አክሱም ምን ያህል ስልጣኔ እንደነበራት ጠቋሚ ነው። ከኩሻይቲክ የሜሮይ አገዛዝ የተወሰደ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ ሀውልቶችን የማቆም ስራ አሁንም ድረስ በአከባቢው ተመሳሳይ ስራዎችን መመልከት ይቻላል። እነዚህ ሀውልትኦች የሚቆሙት በመሠረታቸው ለሚቀበሩ ንጉሳዊ ቤተሠቦች እንደሆነም ታውቋል። በዚህም ከፍተኛ ስልጣን የነበራቸው መሳፍንቶች መቃብር ላይ የሚቆሙት ሀውልቶች በብዛት በተፈለፈሉ የሀሰት በር እና መስኮቶች ያጌጡ ናቸው። እንዲሁም የሟቹ ንጉሳዊነት በቀነሠ ቁጥር በመቃብሩ ላይ የሚቆሙት ሀውልቶችም ውበት (የሚፈለፈሉት የሀሰት በር እና መስኮት መሠል ቅርጾች ብዛት) በዚያው ልክ ይቀንሳል። ለዚህም ነው ብዛት ያላቸው ቅርጽ አልባ ሀውሎቶችን በየቦታው መመልከት የሚቻለው። ትልልቅ የሚባሉት ደግሞ አነስተኛ ቁጥር አላቸው። ከሀውልቶች ሁሉ በመጨረሻ አክሱም ላይ ማለትም በ4ኛው ክፍለ ዘመን እንደቆመ የሚታወቀው የንጉስ ኢዛና ሀውልት ነው። ኢዛና ይህን ጣኦታዊ የሆነ ሀውልቶችን የማቆም ስራ እንዲቆም እና ክርስቲያናዊነት በኢትዮጵያ እንዲስፋፋ በግሉ ክርስቲያን በመሆን ጥሯል። አብዛሀኛዎቹ ትክል ድንጋዮች በመሰረት ጥንካሬ ማነስ የወደቁ ሲሆን ከነዚህም መካከል ተጠቃሽ የሚሆነው በእርዝመቱ ተወዳዳሪ የሌለው (የ33 ሜትር ርዝማኔ ያለው) ታላቁ ሀውልት በመሬት ላይ መውደቁ ነው። በሀውልቶቹ ላይ የደረሱት ችግሮች ብዙ ናቸው። ከነዚህም ውስጥ በተደጋጋሚ የሚከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ (የአክሱም ከተማ ለመሬት መንቀጥቀጥ በአንፃራዊ ሁኔታ የተጋለጠች ነች። በ19ኛው ምዕተ-አመት ከዋና ዋናዎቹ የንጉስ ሀውልቶች መካከል የንጉስ ኢዛና ሀውልት ብቻ ሳይወድቅ ተገኝቷል። በ1928 ዓ.ም ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረችበት ጊዜ ይህን ሀውልት በጊዜው በነበረው የፋሽስት ኢጣሊያ ገዝ ትዕዛዝ መሰረት የጣልያን ወታደሮች የኣክሱምን ሓውልት ከወደቀበት ኣንስተው ወደ ሮም ወሰዱት። በዚህ ጊዜ የፋሺስት አገዛዝ እንደ ጦር ምርኮ እና የሮም ግዛት መስፋፋት ምልክት አድርጎ በመውሰድ በሮም አደባባይ ላይ እንዲተከል አድርጓል (ምንም እንኳን አገዛዙ በአምስት አመታት ወስጥ የነበረ ቢሆንም ይህም እ.ኤ.አ. ከ1935 በ1941 ንጉሠ ነገስት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ወደ ኢትዮጵያ እስከተመለሱበት ጊዜ ያለው ማለት ነው)። ሁለተኛው የዓለም ጦርነት እንዳለቀ ጣልያን የዘረፈችውን የኣክሱም ሃውልት ለኢትዮጵያ እንድትመልስ በተስማማችው መሠረት ላለመፈጸም እስከ የካቲት ፲፱፻፷፮ ዓ.ም. ብዙ ግለሰቦች ቢማጸኑም ኣሻፈረኝ ኣለች። የመጨረሻውም ምክንያት ጣልያን ገንዘብ፣ ኣሜሪካ ኣውሮፕላን ስለከለከሉ ነበር። በእነዚህ ምክንያቶች ያልተደሰቱት ዶ/ር ኣበራ ሞላ ኢንተርኔትን በመጠቀም የመላኪያ ገንዘብ ለማስባስብና ሐውልቱንም በትናንሹ ኣስቆርጦ መላክ እንደሚቻል ለጣሊያኖች ካሳወቁ በኋላ ኣጣብቂኝ ውስጥ የገቡት ጣልያኖች እራሳቸው ወጪውን ከፍለው ከወሰዱበት እንደሚመልሱት ተስማሙ። በእዚሁ መሠረት የጣልያን መንግሥት ወደ ኣሥር ሚሊዮን ዶላር ኣውጥቶ ሐውልቱ ኣክሱም ከተማ ተመልሶ ተተክሎ ነሓሴ ፳፱ ቀን ፳፻ ዓ.ም. ተመርቋል። የውጭ መያያዣዎች የሓውልቱ ከሮም ወደ ኢትዮጵያ ኣመላለስ ሥነ ቅርስ
13958
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%B3%E1%8A%85%E1%88%A3%E1%88%A5%20%E1%8C%8D%E1%88%AD%E1%8C%8D%E1%88%AD
የታኅሣሥ ግርግር
የታኅሣሥ ግርግር በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ዓመቱ በገባ በአራተኛው ወር ላይ የተከሰተው የታኅሣሥ ፲፱፻፶፫ቱ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ፤ የአገሪቷ መጭው ዕድሏ ፊቱን ገለጥ ያደረገብት ሁኔታ ነበር። ለምን? ከ፲፱፻፷፮ቱ አብዮት በፊት ዙፋኑን ክፉኛ ያናጋ ተቃውሞ ቢኖር፤ እንዲያውም የአብዮቱ ምሥረታ፣ በኢትዮጵያ “ዘመናዊ” ታሪክ ውስጥ ወሳኝ የሆነ የፖለቲካ ተቃውሞ ምዕራፍ መክፈቻ ሊባል የሚገባው ይኼው የአምሳ ሦስቱ ሙከራ ስለሆነ ነው። ከዚያ በፊት ዙፋኑ “የማይደፈር፣ የማይሞከር”፤ ንጉሠ ነገሥቱ የማይፈተን መለኮታዊ ሥልጣን እና እንደ ሥርወ መንግሥታቸው አመጣጥ “ሰሎሞናዊ ጥበብ”ን የተቀዳጁ ናቸው የሚባለውን ዕምነት እውን እንዳልሆነ የተገነዘብንበት የታሪክ ምዕራፍ ስለሆነ ነው። ከዚህም አልፎ በአፍሪቃ አኅጉር ከንስር ወይም ግብጽ ስኬታማ መፈንቅለ መንግሥት ተከትሎ የተጸነሰው ሁለተኛው ሙከራ ነበር። በሌላ አመለካከት ደግሞ ሙከራውን በጥምር ያቀነባበሩት ሁለቱ ወንድማማቾች ተምሳሌት የስድሳ ስድስቱን አብዮት በወታደርዊና የሲቪል ገጽታዎች መንታ ጥምርነቱ፣ የሚያንጸባርቅም ፈር ቀዳጅ ድርጊት ሆኖ እናገኘዋለን። «የዓድመኞቹ ዓላማ መንግሥቱን ገልብጠው አንድ መንግሥት ለማቋቋም፣ አልጋ ወራሻችንን ምክንያት አድርጎ ለመስበክ የተቻላቸውን ያህል በብዙ መንገድ ሠርተዋል። ግን ዓላማው የሚበልጠው የነሱን አምቢሲዮን መሙላት፣ የቀረውን የሕዝቡን ያታለሉበት ነገር ሁሉ እኛ ከፈራነው ነገር የወጣ አንድም ነገር የለም።»ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ ከግርግሩ ክሽፈት በኋላ ለውጭ ጋዜጠኞች ከሰጡት ቃለ ምልልስ። የ፲፱፻፵፰ ዓ/ም ሕገ መንግሥት በ ፲፮ኛው ክፍለ ዘመን የጣልያን ተወላጁ ኒኮሎ ማክያቬሊ ሲጽፍ፣ “መገንዘብ ያለብን፣ አዲስ ስርዓትን በመሪነት ማስተዋወቅ ከሁሉም የበለጠ ፈታኝ ሥራ፤ የምሥረታው ተግባርም እጅግ አድካሚ የሆነ እና ውጤቱ ያልተረጋገጠ በመሆኑ የሚወዳደረው ነገር የሌለው ነው” ይላል፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በድሮው ስልት አዲስ ስርዓትን ለማስተዋወቅ ሞከሩ። እሳቸው ባለፈው ምዕተ ዓመት የተወለዱና ባለፈ ስርዓት ያደጉ ሲሆኑ “በስልጣኔ እርምጃ” ላይ ጉዞዋን የጀመረችው የኢትዮጵያ ልጆች ግን አብዛኛዎቹ ከጣልያን ወረራ በኋላ የተወለዱ ነበሩ። “ለአገራችሁ የሥልጣኔ እርምጃ ተግታችሁ ሥሩ፣ አገልግሉ!” ይሏቸው አልነበረም? ታዲያ “ወጣቱ ትውልድ” “ለአገር አንድነትና ብልጽግና” ብሎ ቢነሳ ያው አይደለም? ከ ፲፱፻፵፰ቱ “ሕገ መንግሥት” በኋላ ግን ወጣቱ ትውልድ ንጉሠ ነገሥቱን እንኳን በ“አዲስ ስርዓት” እና ሂደት ሊያሻሽሉ ቀርቶ እንዲያውም ለሥልጣኔ ሳንካ/ ጋሬጣ/ እንቅፋት ናቸው ብሎ አመነ። የአርባ ስምንቱማ ሕገ መንግሥት የተሻሻለ፤ ኢትዮጵያን ከዘመኑ ጋር የሚያጣምር ተብሎ ነበር የታወጀው። በውስጡ የተደነገጉት ሕጎች ግን ቁጥራቸው ከሢሶ በላይ የሚሆኑት ስለ ንጉሠ ነገሥታዊው ቤተሰብና የዘውዱን አወራረስ የሚመለከት እንጂ ወጣቱ እና የተማረው ወገን እንደጓጓው ኢትዮጵያን እንደነ ብሪታንያ እና እንደነ ጃፓን ወደ ሕገ መንግሥታዊ ንጉዛት የሚቀይር አልነበረም። ንጉሠ ነገሥቱ ፍጹም የሆነ ሥልጣን እንደያዙ የሚቆዩበት መሣሪያ ነበር። ይባስ ብሎ ይኸው ሕገ መንግሥት እንኳን የንጉሠ ነገሥቱን ሥልጣን ቀንሶ ለሕዝብ ሊያስረክብ ቀርቶ እንዲያውም የንጉሠ ነገሥቱ ሥልጣን “መለኮታዊነቱን” በማስረገጥ የእንደራሴው ምክር ቤት አባላት እንደተለመደው በሹመት እንጂ በሕዝብ ምርጫ እንደማይሰየሙ አረጋገጠ። ወጣቱ ትውልድ በሚያየው የኤሊ እርምጃ እና ለዚህም ምክንያት ናቸው ብሎ ባመነባቸው በንጉሠ ነገሥቱና አስተዳደራቸው እጅግ ተደናገረ። እነዚህ ወጣት መሪዎች፣ አንዳንዶቹም ውጭ የተማሩ የጥንታዊው ስርዓት ባለሥልጣናት ልጆች ቢሆኑም እርምጃው እንዲፋጠን፤ ዘመናዊ አዲስ ስርዓት እንዲመሠረት ያላቸውን ምኞትና ዓላማ ለማራመድ ሲሹ በግድ የንጉሠ ነገሥቱና የስርዓታቸው ተቃራኒ ኃይሎች መሆናቸው አልቀረም። እውነትም ከዚህ በፊት እነ ቢትወደድ ነጋሽ በዛብህ፣ ብላታ ታከለ ወልደሐዋርያት፤ ደጃዝማች በላይ ዘለቀ እና የመሳሰሉ የንጉሠ ነገሥቱን ሥልጣንና ስርዓት ተፈታትነዋል። ነገር ግን ከሞት በስተቀር ያተረፉት ነገር ወይም ያመጡት ለውጥ አልነበረም። አሁን ግን በተማሩና “ተራማጅ” በተባሉ ወጣት ትውልድ የመሚመራው ቅራኔ ልዩ እና ዘላቂ መሆን ይኖርበታል ብለው ተማምነዋል። መንግሥቱ ንዋይ በ ፲፱፻፰ ዓ/ም አዲስ አበባ ላይ አራዳ ጊዮርጊስ ገዳም ሠፈር አካባቢ ተወለዱ። አባታቸው ዓለቃ ንዋይ የደብሩ ዓለቃ ነበሩ። መንግሥቱ በተወለዱ በስምንት ዓመታቸው በ፲፱፻፲፮ ዓ/ም ታናሽዬው ገርማሜ ንዋይ ተወለዱ። ሁለቱም ትምሕርታቸውን በ ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ተከታትለው አዲሱ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት ሲመሰረት ወደዚያ ተዛውሩ። የገነት ጦር ትምሕርት ቤት ሲከፈት ደግሞ፣ መንግሥቱ ንዋይ ተመልምለው ከገቡት ዕጩ መኮንኖች አንዱ ነበሩ። ሌሎች (በኋላ ጄነራሎች) እንደነ አቢይ አበበ፣ አሰፋ አያና፣ ኢሳያስ ገብረሥላሴና ከበደ ገብሬ በዚሁ ትምሕርት ቤት ከመንግሥቱ ጋር የነበሩ ዕጩ መኮንኖች ናቸው። መንግሥቱ ከዚያው የጦር ትምሕርት ቤት በመቶ አለቃ ማዕረግ ተመርቀው ሲወጡ ወዲያው የጠላት ኢጣልያ ጦር አገሪቱን ይወርና እሳቸው ከሌሎች ጓዶቻቸው ጋር ወደማይጨው ዘምተው ግዴታቸውን ተውጥተዋል። ጠላትም ድሉን ሲቀዳጅ እና ንጉሠ ነገሥቱ ሲሰደዱ መቶ አለቃ መንግሥቱ በዚያን ጊዜ የኢትዮጵያ መንግሥት ወደሸሸበት ነቀምት ሄደው እዚያ “ጥቁር አንበሳ” የሚባለውን ማኅበር መሥራች አባል ናቸው። ከጥቂት ጊዜም በኋላ ከጓደኞቻቸው ጋር ወደጅቡቲ ተሰደዱ። በ፲፱፻፴፪ ዓ/ም ንጉሠ ነገሥቱ ተመልሰው ካርቱም ሲገቡ እነኚህን ስደተኛ መኮንኖች ከጅቡቲ ወደካርቱም እንዲመጡ ይደረግና መንግሥቱ ንዋይ ከነ ሙሉጌታ ቡሊ፣ ነገሠ ወልደሐና፣ ወልደማርያም ኃይሌ፣ ዘውዴ ገበሳ እና ታምራት ዘገየ ጋር ሆነው ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ተቀላቀሉ። ወዲያውም ከእሳቸው ጋር በ፲፱፻፴፫ ዓ/ም አብረው ወደኢትዮጵያ በድል ሲገቡ በክብር ዘበኛ ውስጥ በጄኔራል ሙሉጌታ ሥር ሻምበል ሆነው ቆዩ። በመስከረም ወር ፲፱፻፵፱ ዓ/ም ኮሎኔል መንግሥቱ ብርጋዴር ጄኔራል ተብለው የክብር ዘበኛ ጠቅላይ አዛዥነትን ተሾሙ። ተራማጅ እና የክብር ዘበኛን ሠራዊት በሰገላዊ ውትድርና ንቃተ ሕሊናውን ለማዳበር ብዙ የጣሩ መኮንን እንደነበሩ ተመስክሮላቸዋል። ገርማሜ የስምንት ዓመት ታናሽ ቢሆንም ከሁለቱ የበለጠ የተፈጥሮ ኮስታራ፣ ትጉሕ ተማሪ እና ስፖርተኛ (በተለይም በእግር ኳስ) እንደነበር ይነገርለታል። ታላቅ ወንድሙንም ተከትሎ አንደኛ ደረጃ ትምሕርቱን በተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት፣ ሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በኮተቤው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትምሕርት ቤት ካጠናቀቀ በኋላ በ፲፱፻፴፭ ዓ/ም ገደማ በልዑል አልጋ ወራሽ መርድ አዝማች አስፋ ወሰን ከሁለት ዘመዶቹ ገርማሜ እና አምዴ ወንዳፍራሽ፣ ሙሉጌታ ስነጊዮርጊስ፣ ሙላቱ ደበበ እና ምናሴ ኃይሌ (በኋላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የነበሩት) ጋር ወደአሜሪካ ለትምሕርት ተላኩ። በዚህ ጊዜ ሌሎቹ ለጉዟቸው ሱፍ ልብስ ሲያሰፉ፣ ገርማሜ (ንዋይ) ግን በርኖስ ይገዛና ይሄንኑ ኮት እና ሱሪ አሰፍቶ ለብሶ ወደ ዊስኮንሲን ዩኒቨርሲቲ ይጓዛል። ከዊስኮንሲን የመጀመሪያ ጉላፑን () ይቀበልና ሊቀኪን ጉላፑን () ደግሞ ከ ኮለምቢያ ዩኒቨርሲቲ በ ደቦሰብ ሰገል () ይቀበላል። አሜሪካ በነበረበት ጊዜም በ”ሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር” ፕሬዚደንት ነበረ። ለሊቀኪን ጉላፑ መመረቂያ ያቀረበው የጥናት ጽሑፍ “የነጮች የሠፈራ ፖሊሲ በኬንያ ላይ ያለው ተጽእኖ " በሚል ርዕስ ሲሆን በጭቆና ቀንበር ሥር የሚኖሩ አፍሪቃውያንን ዕሮሮ የሚያስተጋባ ጽሑፍ ነው። ትምሕርቱን እስከ ዲበሲን ጉላፕ () ደረጃ ለመከታተል ቢፈልግም ወደኢትዮጵያ እንዲመለስ በተደረገለት ጥሪ መሠረት በ፲፱፻፵፮ ዓ/ም አገሩ ተመልሶ ሲገባ መጀመሪያ በአገር ግዛት ሚኒስትር ውስጥ የደጃዝማች (በኋላ ራስ መስፍን ስለሺ በኋላም የሚኒስቴሩ የራስ አበበ አረጋይ ዋና ጸሐፊ ሆኖ ሲያገለግል ቆየ። እዚሁ አገር ግዛት ሚኒስቴር ውስጥ በነበረበት ጊዜ በአፍሪቃ አኅጉር የመጀመሪያው መፈንቅለ መንግሥት በንስር የተሳካበት ጊዜ ነበር። ገርማሜም ለኮሎኔል ናስር መንግሥት በድብቅ “እባካችሁ ስለመንግሥታችሁ አቋም እና አመሠራረት ማብራሪያ ላኩልን” የሚል ደብዳቤ መላኩ ሲደረስበት በንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት እና በጊዜው ባለሥልጣኖች ላይ ምን ያህል ሽብር እና የእምነት ጉድለት እንደጣለ መገመት ይቻላል። አለባበሱ ሁሌም በካኪ ልብስና ቀይ ክራባት ስለነበረም “ወልፈናኝ” () የሚል ቅጽል ስም ከማትረፉም በላይ ለአብዮታዊ መንግሥቶች ከጻፈው ደብዳቤ ጋር በትንሹ የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት ጥርጣሬ፣ በተጨባጭ ሁኔታ ግን ታላቅ ትኩረት እንዲሰጠውና በ”እንግልት ሥፍራ” መንፈሱ መሰበር እና ሎሌነቱ መፈተን እንዳለበት ወሰኑ። ስለዚህም በተከታታይ በስውር ግዞት የሩቅና ፈታኝ ግዛቶች አስተዳዳድሪ እየተደረገ ይሾማል። የገርማሜ ንዋይ የመጀመሪያው መፈተኛ የወላይታ አውራጃ ገዥነት ነበር። እሱ ግን ይሄንን የግዞት ቦታ የፍትሓዊ አስተዳደር ሙከራ ጣቢያ በማድረግ ብዙ “ፍሬያማ” ሥራዎችን ሠርቷል። ለምሳሌ፦ • በሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎች የሚማሩበትን ትምሕርት ቤቶች በመሥራት • የሥፍራ ዕቅድ በመጀመርና የጭሰኝነትም ውልም በጽሑፍ በመደንገግ የጭሰኛውን መከራ ከፈለለት በንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት በኩል ግን፣ እንኳን መንፈሱ ሊሰበር ቀርቶ እንዲያውም በአውራጃው ሕዝብ የተወደደ ሲሆን እንግልቱ አንሷል እንደማለት ያህል ይመስላል፣ በዘመኑ የእንግሊዝ መንግሥት የኢጣልያ ሶማልያን እና በጊዜው በሞግዚትነት ያስተዳድር የነበረውን የኦጋዴንን ግዛት አጣምሮ “ታላቋ ሶማልያ” በሚል አንድ አድርጎ ከኢትዮጵያ እጅ ለመፈልቀቅ በሚዶልትበት ፈታኝ ጊዜ፣ ገርማሜን የጅጅጋ አውራጃ ገዥ ያደርጉታል። እሱ ግን የኢትዮጵያ ሱማሌዎችን ሕይወት ለማሻሻል በወሰዳቸው እርምጃዎች ተወዳጅነትን አገኘ እንጂ እንደተገመተው መንፈሱም አልተሰበረ፣ ሥራው አልከሸፈም። መንግሥት በዚህም በጠረፍ አስተዳደሩም ላይ ጣልቃ እየገባበት ሊያደንቅፈው መሞከሩን አልተወውም። ያንጊዜ ነው ማዕበሉን መለወጥ አማራጭ የሌለው ተግባር መሆኑን የተረዳው። ወንድሙንም ለዚሁ ዓላማ ማነሳሳት የጀመረው ያኔ ነው። የሙከራው ጥንሰሳ መንግሥቱ ንዋይ ለፖሊስም ሆነ በሕይወታቸው ላይ ለፈረደባቸው ችሎት እንደገለጹት፣ ከ ፲፱፻፵፯ ዓ/ም ጀምሮ ንጉሠ ነገሥቱን እየተከተሉ በየከተማው፣ በየአውራጃውና በየወረዳው ሲዘዋወሩ የአቤቱታ አቅራቢው ሕዝብ ብዛትና በአዋጅ የሚነገረው ሁሉ ተግባር ላይ አለመዋሉ ያሳስባቸው እንደነበር ተንትነዋል። የመፈንቅለ መንግሥቱም ሦስተኛ አባል የነበሩት የንጉሠ ነገሥቱ ልዩ ካቢኔ ጸጥታ ጉዳይ ኃላፊ የነበሩት ሌተና ኮሎኔል ወርቅነህ ገበየሁም እንዲሁ በፍትሕ ዕጥረት ምክንያት ብሶት እንደተሰማቸው ይነገራል። አራተኛው አባል ብርጋዴር ጄነራል ጽጌ ዲቡ የብርጋዴር መንግሥቱ የቅርብ ወዳጅ ከመሆናቸውም ሌላ የፖሊስ ሠራዊቱ ዋና አዛዥ ነበሩ። ጽጌና መንግሥቱ አብረው ይውላሉ አብረው ያመሻሉ። በፖሊስ ሠራዊት ፈጥኖ ደራሽ ግቢ መኮንኖች ክበብ ነው የሚውሉት የሚያመሹት። ወንድማማቾቹ አባታቸው ዓለቃ ንዋይ በሞቱ በሁለተኛው ወር በአንድ ድግስ፤ መንግሥቱ ከወይዘሪት ከፋይ ታፈረ ጋር ገርማሜ ደግሞ ከወይዘሪት አያልነሽ ዘውዴ ጋር የካቲት ፱ ቀን ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ተዳሩ። በሚቀጥለው ዓመትም ሚያዝያ ፳፪ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም በሱሉልታ የተካሄደው የክብር ዘበኛ ሠራዊት የጦር ታክቲክ ትልቅ የማስጠንቀቂያ ደውል መሆኑን እና መፈንቅለ መንግሥቱ የዚያን ዕለት እንደተጀመረ እነ አቶ መኮንን ሀብተወልድ ገምተዋል ይባላል። ለማንኛውም የሙከራው ጥንሰሳ ተደርሶበት ነበ፤። አልፎ ተርፎም ንጉሠ ነገሥቱን የጸጥታና ስለላ ክፍል ሃላዊዎቻቸው አስጠንቅቀዋቸው ነበር ቢባልም፣ “አያደርጉትም” በሚል ንቀትም ይሁን ወይም ደግሞ በዕርግጥ የሚከሰት ተግባር ከሆነ ደግሞ እራሳቸውን ከጥቃት አግጣጫ ለማስወገድ ያቀዱትም የ”ሰሎሞናዊ ጥበብ” ሊሆን ይችላል፤ ብቻ ንጉሠ ነገሥቱ ኅዳር ፳፩ ቀን ለጉብኝት መጀመሪያ ወደምዕራብ አፍሪቃ ቀጥሎም ወደብራዚል በረሩ። ለእድምተኞቹ ይሄ እንከን ወይም ተወዳዳሪ የሌለው አመቺ ሁኔታን ፈጠረላቸው። የታኅሣሡ ጉሽ ሙከራው ማክሰኞ ታኅሣሥ ፬ ቀን ተጀመረ። ለትላልቅ መሳፍንት፣ መኳንንቶችና ዋና ሚኒስቴሮች “እቴጌ ታመዋልና በአስቸኳይ ወደቤተ መንግሥት ይምጡ” የሚል የስልክ ጥሪ መልክት ተላለፈ። እነ ራስ ስዩም መንገሻ፣ ራስ አበበ አረጋይ፣ አባ ሐና ጅማ፣ መኮንን ሀብተወልድ እና ሌሎችም በተቀበሉት ጥሪ መሠረት ቤተ መንግሥቱ ሲደርሱ ከእቴጌይቱ እና ከአልጋ ወራሽ ጋር ቁጥጥር ስር ዋሉ። የጦር ሠራዊቱ ኤታ ማጆር ሹም ሜጀር ጄነራል መርድ መንገሻ እና የምድር ጦር አዛዡ ሜጀር ጄነራል ከበደ ገብሬ ግን በተደጋጋሚ ቢጠሩም አሻፈረኝ ብለው አፈንግጠው ቀሩ። ዕሮብ ታኅሣሥ ፭ ቀን ወንድማማቾቹ መፈንቅለ መንግሥቱን ለሕዝብ ሲያስተዋውቁ፣ ለማስተላለፍ የፈለጉት ዐቢይ መልእክት ኢትዮጵያ በቅርብ ነጻ ከወጡት የአፍሪቃ አገሮች እንኳን ስትነጻጸር ምን ያህል ወደኋላ እንደቀረችና የመፈንቅለ መንግሥቱ ሙከራ የሀገሪቱን የቀድሞ ዝናና ክብር ለማደስ መሆኑን ነው። የሰፊው ሕዝብ ብሶት የቆረቆራቸው መሆኑን በመግለጽ፣ ፋብሪካዎች ለማቋቋምና ትምሕርት ቤቶች ለመክፈት ቃል ገቡ። የለውጥ ፈላጊ ናቸው የሚባሉትን ልዑል ራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መሾማቸውንና አልጋ ወራሹን አስፋ ወሰንን (“አስገድደው”) በማስማማትም መንግሥት በቆረጠላቸው ደመወዝ እየተዳደሩ ለሕገ መንግሥት የሚገዙ ንጉሥ ሆነው እንደሚያገለግሉ እራሳቸው ለሕዝቡ በራዲዮ እንዲያስተላልፉ አደረጉ። ይሄ የአልጋ ወራሹ መልዕክት በገርማሜ ንዋይ፣ በሌተና ኮሎኔል ወርቅነህ ገበየሁና ባልደረቦቻቸው የተዘጋጀ ንግግር ሲሆን በከፊል እንደዚህ ነበር፦ “…ድንቁርናን ከመካከላቸው አጥፍተው በአእምሯቸው መራቀቅና በኑሮ ደረጃው እየገፉ የሚሄዱ የዓለም ሕዝቦች ላይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሊያደርሰው የሚችል የማይፈጸም የቃል ተስፋ መስማት ሳይሆን እውነተኛ ተግባር ላይ የዋለ የሕዝብ የአእምሮና የኑሮ እድገት የሀገር ኃብት ልማት ፕሮግራም እስከዛሬ ድረስ ተዘርግቶ ካለማየቱም በላይ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ነጻነታቸውን ያገኙ የአፍሪቃ አገሮች እንኳን ሳይቀሩ በሚፈጽሙት የስልጣኔ እርምጃዎች የኢትዮጵያን ሕዝብ እየቀደሙና ወደኋላ እየጣሉ ወደፊት የሚገሰግሱ መሆናቸው ለኢትዮጵያ ዕለት በዕለት ገሃድ እየሆነለት ሄደ። ይሄም ሁኔታ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ የኢትዮጵያን ሕዝብ የረጅም ተስፋ መጨረሻ ላይ አላደረሰውም። ይህም ከመሆኑ የተነሳ ከጥቂት ጊዜ ወዲህ የተጀመረው የሕዝብ እንቅስቃሴ እነሆ ዛሬ ሥልጣንን ጨብጦ ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለሀገሪቱም መድኅን ከመሆን ደረጃ ላይ መድረሱን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ልገልጽላችሁ ዕድል በማግኘቴ ደስታዬ ፍጹም ነው።…….” ይህ በእንዲህ እንዳለ ዋና ተቃራኒዎቹ፤ አንደኛው ከሻለቃነት ማዕረግ በአንድ ጊዜ ወደ ብርጋዴር ጄነራልነት የተተኮሱት ሜጀር ጄነራል መርዕድ መንገሻ ሲሆኑ ሌላው ደግሞ ሜጀር ጄነራል ከበደ ገብሬ ያለመያዛቸው ለተቃራኒው ኃይል ጊዜ የሰጠና በመጨረሻም የሙከራውን መክሸፍ ምክንያት ሆኑት ከሚባሉት ዐቢይ ጉዳዮች ዋናው ነው። ከመኳንንቱ መኃል ደግሞ የሕዝብ እንደራሴዎች ሸንጎ ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዳጃዝማች (በኋላ ልዑል ራስ) አሥራተ ካሳ ነበሩ፡ እነኚህ ሁለት ጄነራሎችን እና የመሳሰሉ ተቃራኒዎችን መንግሥቱ ንዋይ ሌሎቹን በቁጥጥር ሥር ባዋሉበት ስልት እንዲመጡ ቢጠይቋቸውም አሻፈረን ብለው መቅረታቸው እጅግ በጣም በጅቷቸዋል። ሌተና ኮሎነል ወርቅነህ ገበየሁ ለመፈንቅለ መንግሥቱ ስኬታማነት እነዚህን ሁለት ጄኔራሎች በአስቸኳይ ቁጥጥር ላይ ማዋል ወሳኝ መሆኑን ደጋግመው ቢያስታውሱም ጄነራል መንግሥቱ ግን “ደም መፋሰስን ያስከትላል” በሚል ዕምነት ውድቅ አደረጉባቸው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስም “ክርስቲያን የሆናችሁ ልጆቼ እንዲሁም የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ…..ትናንትና አንዳንድ የክብር ዘበኛ ሠራዊት አባላት….ሀገራቸውን ክደዋል።….እነኚህን ከሃዲዎች አትመኑ አትከተሏቸው። በተሰጠኝ ሥልጣን አውግዣችኋለሁ…” የሚለውን መልክታቸው በሠፊው ተሰራጨ/ተበተነ። አቶ ጌታቸው በቀለ “” በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ፣ ኮሎነል ወርቅነህ "ስለ መፈንቅለ መንግሥቱ መጠንሰስ የሰማሁት ከተጀመረ በኋላ ነው። አሁን ተቃዋሚ ብሆን ጠንሳሾቹ ይገሉኛል። ከነሱ ጋር ሆኜ ለለውጥ ስዋጋ ብሞት ይሻለኛል ብዬ ወስኛለሁ።" አሉኝ ብለዋል መንግሥቱ ንዋይና ሁለቱ ጓደኞቻቸው ስላልተያዙት ሁለት ጄነራሎች የነበራቸው ግምት በጣም አነስተኛ ሲሆን ጄነራል መርድ የተገመቱት በአዲሱ መንግሥት ውስጥ ስለሚኖራቸው የሥልጣን ክፍያ ዋስትና ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸው ሲሆን፤ በጥሩ ኢትዮጵያውነት የተወሱት ከበደ ገብሬ ደግሞ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ደህንነት ባላጋራ እንደማይሆኑና ከመርዕድ መንገሻ ጋር እንዳልተስማሙ በተጨባጭ መግለጫ የተደገፈ ነበር። ሆኖም የነኚህን አፈንጋጭ ጄነራሎች ከሥልጣን መሻር በራዲዮ አስነገሩ። ሐሙስ ታኅሣሥ ፮ ቀን የነጄነራል መርድ ተቃራኒ ኃይል ዝግጅቱን ጨርሶ በዚያው ዕለት ከቀትር በኋላ በዓየር እና በታንክ ጭምር የተፋፋመ ውጊያ ሲጀምር መንግሥቱ ንዋይ መምሪያ ክፍላቸውን ወደ ገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ያዛውራሉ። ዓርብ ታኅሣሥ ፯ ቀን የሙከራው ኃይል እየተዳከመ በአንጻሩ ደግሞ ተቃዋሚዎቻቸው እያደር እየጎለመሱ መሄዳቸውን የተገነዘቡት ሽብርተኞች በቁጥጥራቸው ላይ የነበሩትን ሃያ መሳፍንት፣ መኳንንት፣ ሚኒስትሮችንና መኮንኖችን ወደ አረንጓዴ ሳሎን ያዛውሩና አልጋወራሹንና አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ለብቻቸው እንዲጠበቁ ያደርጋሉ። ጄነራል ጽጌ ዲቡ ወዲያው ከተቃራኒ ወገን በተተኮሰ ጥይት ሲገደሉ፣ እነ ጄነራል መንግሥቱ የያዟቸውን እስረኞት ረሽነው ለማምለጥ ወሰኑ። ከነዚህ እስረኞች መሃል የነበሩት ብርጋዴር ጄነራል መኮንን ደነቀ “እኔ አውቆ ይሆን ሳያውቅ እንደሆነ አላውቅም፣ ነገር ግን መጀመሪያ ጥይት የተተኮሰው በሙሉጌታ ላይ ነው።” “መንግሥቱ ንዋይ ውጡ ሲል ሲወጡ ከጀርባቸው ተኩስባቸው ብሎ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር መንግሥቱ። በኋላ ተነሱና ውጡ አሉ፡ አባ ሐና እኔ ቤቱን አውቀዋለሁ ከዚህ የተሻለ ቦታ የለም ሲሉ መንግሥቱ “ታዲያ አትሏቸውም?” ሲል ተኩሱ ተከፈተ።” ይላሉ። መንግሥቱ ንዋይ ግን በ የካቲት ወር ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ለፍርድ ቤት በሰጡት ቃል “እኔ ግደሉም አላልኩም እራሴም አልተኮስኩም” ብለዋል። ያም ሆነ ይህ፣ ከሀያዎቹ መኻል እነ ሙሉጌታ ቡሊ፤ ራስ ሥዩም መንገሻ፤ ራስ አበበ አረጋይ፤ አቶ መኮንን ሀብተወልድ፤ አባ ሐና ጅማ፤ አቶ አምደሚካኤል ደሳለኝ፤ ብላታ ዳዊት ዕቁበ እግዚ፤ አቶ ገብረ ወልድ እንግዳ ወርቅ፣ ብላታ አየለ ገብሬ፤አቶ ታደሰ ነጋሽ፤ በጠቅላላው አሥራ አምስቱ ሲገደሉ፣ ሦስቱ ቆስለው ራስ አንዳርጋቸው መሳይ እና አንድ ሌላ ሰው ደግሞ ምንም ሳይነካቸው ተርፈዋል። ተቆሰሉትም አንዱ በአሥራ ሁለት ጥይት ተመተው የተረፉት ብርጋዴር ጄነራል መኮንን ደነቀ ናቸው። ጽጌ ዲቡ ከጦር ሠራዊት ኃይሎች ጋር ሲታኮሱ ቀደም ብለው ሲሞቱ፣ ኮሎኔል ወርቅነህ ደግሞ በተከበቡ ጊዜ “እጄን አልሰጥም ብለው” ራሳቸውን አጠፉ። መንግሥቱና ገርማሜ ግን በቤተ መንግሥቱ ጋራዥ በኩል ሾልከው ወደቀጨኔ መድሃኔ ዓለም በኩል ጫካ ለጫካ ኮበለሉ። ከሙከራው በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ በማግስቱ ቅዳሜ ታኅሣሥ ፰ ቀን በአስመራ በኩል አድርገው ብዙም ወደአልተረጋጋችው አዲስ አበባ ከተማ ሲገቡ ወዲያው የወንድማማቾቹን ፎቶግራፍ የያዘ ማስታወቂያ በሠፊው ተሰራጨ። “የብዙዎችን ደም በግፍ ያፈሰሱት ከሐዲዎች የመንግሥቱ ንዋይና የገርማሜ ንዋይ ፎቶግራፎች እነዚህ ናቸው። ……..ጢማቸውን በመላጨት ወይም በማሳደግ ወይም በሌላ ዘዴ ይጠቀሙ ይሆናል። እነሱን ይዞ ለመጣ ታማኝ፣ በእያንዳንዳቸው አሥር ሺህ ብር/$ 10000 እና ልዩ ሽልማት ይሰጠዋል።” የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ታኅሣሥ ፲፭ ቀን ወንድማማቾቹና ባልደረባቸው ሻምበል ባየ ጥላሁን ከአዲስ አበባ ድሬ ጨለባ በሚባል ሥፍራ ወደሚገኝ የዘመዳቸው እርስት በማምራት ላይ ሳሉ ነው የተከበቡት። እዚሁ ሥፍራ በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ሻምበል ባየ እና ገርማሜ ሲገደሉ መንግሥቱ ነዋይ ግን ክፉኛ ቆስለው ይያዛሉ። የሁለቱ ሟቾች አስከሬን አዲስ አበባ ቤተ መንግሥቱ ደጃፍ ላይ ካደረ በኋላ በማግሥቱ ከኮሎኔል ወርቅነህ ገበየሁ አስከሬን ጋራ ምኒልክ አደባባይ ላይ ተሰቅሎ ዋለ። መንግሥቱ ንዋይ ቆስለው ከተያዙ በኋላ ከወር በላይ በህክምና ቆይተዋል። ከህክምናውም በኋላ የካቲት ፫ ቀን ለፍርድ ሲቀረቡ አንድ ዓይናቸው ድሬ ጨለባ ላይ የጠፋ ከመሆኑም በላይ ሁለተኛውም አስተማማኝ አልነበረም፡፡ በዚሁ ችሎት ላይ “መጀመሪያ ላይ አንድ ደረጃ ባላቸው የተያያዘ፤ በተማሩና አዲስ መንፈስ ባላቸው ኢትዮጵያውያኖች መንግሥት ለማቋቋም ነው ያሰብኩት። ከዚያ በኋላ ጃንሆይ ይጠየቃሉ። ጃንሆይ ይጠየቁና በእንግሊዝ መንግሥት ደረጃ ወይም ፖሊሲ መሠረት በመንግሥት ጉዳይ ውስጥ አጠቃላይ ሳይገቡ ፓርላማው ራሱ ነው የሚገዛው። ቤተ መንግሥቱን የሚያዘው ፓርላማ ነው።” ብለዋል ፍርድ ቤቱ መጋቢት ፲፱ ቀን ውሳኔውን ሰጠ። ጄነራሉ ይግባኝ ይሉ እንደሁ ሲጠየቁ ከዚህ የሚከተለውን እንደትንቢት የሚቆጠር ምላሽ ሰጡ። ”እናንተ ዳኞች! የበየናችሁብኝን የሞት ፍርድ ያለይግባኝ ተቀብያለሁ። ይግባኝ ብዬ የሚመለከትልኝ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቢሆን ኖሮ ይግባኝ ማለት በፈልኩ ነበር። ነገር ግን ይህ እንደማይሆን አውቃለሁና የዓፄ ኃይለ ሥላሴን ፊት ለማየት አልፈቅድም። በእግዚአብሔር ስም በተቀመጣችሁበት የፍርድ ወንበር ላይ ከመቀመጣችሁ በፊት በእኔ ላይ የምትሰጡትን ፍርድ ታውቁት እንደነበር ሳስበውና ፍርድ እስከዚህ መድረሱን ስታዘብ ኀዘኔ ይብሳል። ለኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነት፣ ነጻነትና እርምጃ የተነሳሁ ወንጀለኛ ነኝ እንጂ ላፋጀው የተነሳሁ ወንበዴ አይደለሁም። ይህን ማድረግ ፈልጌ ቢሆን ኖሮ ማንም የማይወዳደረው ሠራዊትና መሣሪያ ሳላጣ ዛሬ ከእናንተ ፊት ለመቆም ባልበቃሁ ነበር። እኔ ከዓፄ ኃይለ ሥላሴ ድንክ ውሾች ያነሰ ደመወዝ የሚያገኙ ሁለት የተራ ወታደሮችን አጣልቼ ለማደባደብና ሀገር ለማፍረስ አለመነሳሳቴን የሚያረጋግጥልኝ ከእናንተ በትዕዛዝ ያገኘሁትን ፍርድ ለመቀበል እዚህ መቆሜ ነው። ከእኔ በፊት በግፍ የፈሰሰው ንፁህ የኢትዮጵያዊያን ደም ብዙ ነው፡፡ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ግፍ ሽልማት በመሆኑ እኔ ለመሞት የመጀመሪያው ሰው አልሆንም፡፡ ሥልጣን አላፊ ነው፡፡ እናንተ ዛሬ ከጨበጣችሁት የበለጠ ሥልጣን ነበረኝ፡፡ ሀብትም አላጣሁም፡፡ ነገር ግን ሕዝብ የሚበደልበት ሥልጣንና ድሃ የማይካፈለው ሀብት ስላልፈለግሁ ሁሉንም ንቄ ተነሳሁ። አሁንም እሞታለሁ፡፡ ሰው ሞትን ይሸሻል ፡፡ እኔ ግን በደስታ ወደሞት እሄዳለሁ፡፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅነት ቀድመውኝ መስዋዕት የሆኑትን አብረውኝ ተነስተው የነበሩትን ጀግኖች ወንድሞቼን ለመገናኝት ናፍቄአለሁ፡፡ የጀመርኩት ሥራ ቀላል አይደለም። ነገር ግን አልተሸነፍኩም። ወገኔ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የጀመርኩትን ሥራ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ፈጽሞ እራሱን እንደሚጠቅምበት አልጠራጠርም። ከሁሉ በበለጠ የሚያስደስተኝ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ልሠራለት ካሰብኳቸው ሥራዎች አንዱ የኢትዮጵያን ወታደር ዋጋና ክብር ከፍ ማድረግ ሲሆን ይህ ኀሳቤ ሕይወቴ ከማለፉ በፊት ሲፈፀም ማየቴ ነው፡፡ ዛሬ መኖራችሁን በማየቴ ነገ መሞታችሁን ረስታችሁ አሜን ብላችሁ ቀናችሁን በማስተላለፍ በመገደዳችሁ በእኔ ላይ ሳትፈርዱ በራሳችሁ ላይ የፈረዳችሁ መሆናችሁን አላስተዋላችሁም፡፡ እኔ የተነሳሁት ከትክክለኛ ህግና ከህሊናችሁ ውጭ ለመፍረድ እንዳትገደዱ ለማድረግ ነበር፡፡ ባጭሩ በእኔ ላይ ለመፍረድ የቸኮላችሁትን ያህል አሥር እና አሥራ አምስት ዓመት የምታጉላሉት የድሀውን ሕዝብ ጉዳይ እንደዚህ አፋጥናችሁ ብትሠሩትና ብትሸኙት ኖሮ የእኔ መነሳት ባላስፈለገ ነበር። ከእናንተ ከዳኞችና የሞት ፍርድ እንድትበይኑብኝ ካዘዛችሁ ሰው ይልቅ ፍርድ ተቀባይ የዛሬው ወንጀለኛ የነገው ባለታሪክ ነኝ። የኔ ከጓደኞቼ መካከል ለጊዜው በሕይወት መቆየትና ለእናንተ ፍርድ መብቃት የመመዘኑን ፍርድ ለመጭው ትውልድ የሚያሳይ ይሆናል፡፡ ዋ ! ዋ ! ዋ ! ለእናንተና ለገዢአችሁ፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ሃሳቤ በዝርዝር ገብቶት በአንድነት በሚነሳበት ጊዜ የሚወርድባችሁ መዓት አሰቃቂ ይሆናል፡፡ በተለይ የአፄ ኃ/ስላሴ የግፍ መንግስት ባላደራዎች ሆነው ድሀውን የኢትዮጵያ ህዝብ ሲገሸልጡት ከነበሩት መኮንን ሀ/ወልድና ገ/ወልድ እንግዳወርቅን ከመሳሰሉት በመንፈስ የታሰሩ በስጋ የኮሰሱ መዠገሮች መካከል ጥቂቶቹን ገለል ማድረጌን ሳስታውስና የተረፉትም ፍፃሜያቸውን በሚበድሉት በኢትዮጵያ ህዝብ እጅ ላይ መውደቅ ሲሰማኝ ደስ ይለኛል፡ በዚሁም መሠረት ጄነራሉ መጋቢት ፳፩ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም በስቅላት ተቀጡ። መንግሥቱ ንዋይ በተከተሉት ጥቂት ዓመታት የንጉሠ ነገሥቱን ስርዓት በመቃወም ለቀጠለው ትግል እና ከአሥራ ሁለት ዓመት በኋላም ስርዓቱን ላወደመው አብዮት ዋና ፈር ቀዳጅና አርአያ ሲሆኑ በወንድማቸው እና በአባታቸው ስም የሰየሟቸው የሁለት ወንድ ልጆች አባትም ነበሩ። ዋቢ ምንጮች ጦቢያ መጽሔት፣ አራተኛ ዓመት ቁጥር 2፣ ጥቅምት 1988 ዓ/ም ጥቁር ደም ጋዜጣ፣ ሁለተኛ ዓመት ቁጥር 64፣ መስከረም 23 ቀን 1992 ዓ/ም የኢትዮጵያ ታሪክ
50224
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%A1%E1%8A%90%20%E1%8C%B4%E1%8C%A5%E1%88%AE%E1%88%B5
አቡነ ጴጥሮስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራነት የሰጠቻቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ በትምህርታቸው እያበረቱ በማስተዳደር ላይ እንዳሉ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. አረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት በግፍ ሀገራችንን ለመውረር ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት በማለት ባሕርን አቋርጦ መጣ ፡፡ አጭር የጀግንነት ታሪካቸውን ዝቅ ብለው ቪዲዮ ክሊፕ ላይ ማዳመጥ ይችላሉ ። ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀገር በመጣ ወራሪ ቀጥተኛ ተጠቂናትና ሊቃውንቷ፣ ገዳማትና አድባራቷ እንዲሁም ንዋያተ ቅድሳቷ በወራሪው የኢጣልያ ኃይል ይጨፈጨፉና ይቃጠሉ ገቡ ፡፡ ይህ ግፍ በዕውቀት ኮትኩታ ባሳደገቻቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲፈጸም ያዩት ብፁዕነታቸው ወራሪውን ኃይል ከኢትዮጵያውያኑ አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎት ሊዋጉት ወሰኑ ፡፡ በመጀመሪያ የወቅቱ የሀገሪቱ መሪ ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ከአረመኔው ፋሺስት ጦር ጋር በመፋለም ላይ የነበረውን አርበኛ ለማበረታታት ወደ ማይጨው በሔዱ ጊዜ ብፁዕነታቸው ተከትለው ሔዱ፡፡ ይሁን እንጂ ንጉሡም ሆኑ ብፁዕነታቸው ከሠራዊቱ ጋር ተቀላቅለው ብዙም ሳይቆዩ የጠላት ጦር በመርዝ የታገዘ ጥቃት በስፋት በመክፈቱ የኢትዮጵያ ሠራዊተ ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ሆነ፡፡ በዚህም የተነሣ ንጉሡ ወደ አዲስ አበባ ሲመለሱ ብፁዕነታቸውም አብረው ተመለሱ ፡፡ እዚሁ እሞታለሁ ብለው እንቢ ያሉት ንጉሡ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ከሌሎች አባቶች ጋር ብፁዕነታቸው ያደረጉት ሚና ቀላል እንዳልነበር ይነገራል ፡፡ በበለጠ ለመረዳት ይህን ይመልከቱ ቆራጥ ውሳኔያቸው ይሁን እንጂ በጠላት የግፍ ጥቃት ክፉኛ ያዘኑት ብፁዕነታቸው በአዲስ አበባ ለመቀመጥ አልፈቀዱም፡፡ በታላቁ የደብረ ሊባኖስ ገዳም ተሰባስበው የቤተ ክርስቲያን አምላክ እግዚአብሔር በኢትዮጵያውያን ላይ የመጣውን ችግር እንዲያስታግስ በጸሎት እየለመኑ ወደ ነበሩት አባቶችና አርበኞች በመሄድ ለሀገርና ለነጻነት መሞት ቅዱስ ተግባር መሆኑን በመስበክ ሁሉም እንዲጋደሉ ማሳሰብ እና ማትጋት ጀመሩ፡፡ ምንም እንኳን ድልን ባይቀዳጅም በእርሳቸው ስብከት የተነሣሡት አርበኞችም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ጠላትን ወግተዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ብፁዕነታቸውም አብረው ነበሩ፡፡ ያጋጠማቸው እክል ብፁዕነታቸው የነበሩበት የአርበኞች ጦር ወደ አዲስ አበባ ቢመጣም ድል ላለመቀዳጀቱ ምክንያቱ የመረጃ ልውውጥ ክፍተት እንደነበር ይነገራል፡፡ ይኸውም “የሰላሌ አርበኞች” ተብሎ የሚታወቀው፣ በነደጃዝማች አበራ ካሣ ይመራ የነበረውና በደብረ ሊባኖስ ጫካዎች ውስጥ መሽጎ የነበረው አርበኛ ጦር በሸንኮራ በኩል ከነበረውና በደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ይመራ ከነበረው አርበኛ ጦር፣ በምዕራብ በኩል ከነበረውና በደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ይመራ ከነበረው አርበኛ ጦር ጋር በአንድ ጊዜ ተንቀሳቅሶ አዲስ አበባ ላይ ወንበሩን አደላድሎ የተቀመጠውን የግራዚያኒን ጦር ሊወጋ ይነጋገራል፡፡ ይሁን እንጂ በስምምነቱ መሠረት ሦስቱም የጦር ኃይል ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት ብሎ ወደ አዲስ አበባ ቢንቀሳቀስም በሦስቱም አቅጣጫ በአንድ ጊዜ ባለ መድረሱ በጠላት ላይ ያደረሰው ጉዳት ቀላል የሚባል ባይሆንም በተናጠል እየተመታ ወደ መጣበት ተመለሰ፡፡ በመጀመሪያ በኮተቤ በኩል የደረሰው የደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ጦር ነበር፡፡ ይህ ጦር የካ ሚካኤል ላይ ሲደርስ ተመትቶ ተመለሰ፡፡ የጠላት ጦር የደጃዝማች ፍቅረ ማርያምን ጦር ወደ መጣበት መልሶ ወደ አዲስ አበባ ሲመለስ የደጃዝማች ባልቻ ጦር በባቡር ጣቢያ በኩል መጣሁ አለ፡፡ እሱንም መትቶ መለሰ፡፡ በመጨረሻ ደግሞ የደጃዝማች አበራ ጦር በእንጦጦ በኩል አድርጎ መጣ ፡፡ እሱም በጠላት ጦር ተመትቶ ተመለሰ ፡፡ የመጨረሻ ውሳኔያቸው በዚህ ዓይነት ሦስቱም ኃይሎች በአንድ ጊዜ ባለማጥቃታቸው ወደየመጡበት ሲመለሱ ከሰላሌ አርበኞች ጋር የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ጠላት ከኢትዮጵያውያኑ ነጥቆ አገሬ ከተማዬ ብሎ በመቀመጥ በመላ ሀገሪቱ የሚያካሒደውን ጭፍጨፋ የሚመራባትንና ትእዛዝ የሚያስተላልፍባትን ከተማ አዲስ አበባን ትተው ለመሄድ አልፈቀዱም፡፡ በመሆኑም “ብችል በኢትዮጵያውያን ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍ በቅርብ ርቀት ሆኖ የሚመለከተውን ሕዝብ በማትጋት በጠላት ላይ እንዲነሳ አደርጋለሁ፤ ካልሆነ ደግሞ እዚሁ እሞታለሁ” ብለው ከአርበኞች ተነጥለው በአዲስ አበባ ቀሩ፡፡ ሰማዕቱ ጴጥሮስ ይሁን እንጂ ጠላት በመላ ከተማዋ ባሰማራቸው በርካታ ባንዳዎች መካከል ብፁዕነታቸው እንዳሰቡት ሊንቀሳቀሱ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ እዚሁ ከተማ ተሰውሬ መኖር አልፈልግም፤ ወደ ገጠር ፊቴን አልመልስም በማለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በወቅቱ የኢጣሊያ እንደራሴ ለነበሩት ራስ ኃይሉ እጃቸውን ሰጡ፡፡ እራስ ኃይሉም ወዲያውኑ ለግራዚያኒ አሳልፈው ሰጧቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በተጠቀሰው ቀን እጃቸውን ከሰጡበት ጊዜ ጀምሮ በጠላት የጥይት እሩምታ በሰማዕትነት እስካለፉበት ጊዜ ድረስ የነበረውን ሂደት ኮርየሬ ዴላሴራ የተባለው የጋዜጣ ወኪል እና የምስራቅ አፍሪካ ዜና መዋዕለ አዘጋጅ የነበረው ፓጃሌ የተባለ ጋዜጠኛ እ.ኤ.አ ሰኔ 15 ቀን 1936 ዓ.ም አዲስ አበባ በነበረ ጊዜ በብፁዕነታቸው የተሰጠውን ፍርድና የተፈፀመውን ግድያ ባየው እና በተመለከተው መንገድ እንደሚከተለው ጽፎ ነበር፡ ሐምሌ 22 ቀን 1928 አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ ፡፡ በዚህ ጊዜ አቡነ ቄርሎስ የተባሉት “ግብፃዊ ጳጳስ ቀርበው ለእስክንድሪያው መንበረ ፓትርያርክ ምክር ቤት ሳታሰማ በአቡነ ጴጥሮስ ላይ አንዳች ነገር ማድረግ አይገባህም” ሲሉ ለግራዚያኒ ነገሩት ፡፡ ምክንያቱም ይላሉ አቡነ ቄርሎስ “አቡነ ጴጥሮስ ታላቅ ሰው ናቸው፡፡ በመሰረቱ ሊያዙ ባልተገባ ነበር፡፡ ከተያዙ ደግሞ ልትገላቸው ትችላለህ፡፡ ነገር ግን በእርሳቸው ላይ የምታደርገውን ነገር ሁሉ ለእስክንድሪያው መንበረ ፓትርያርክ ምክር ቤት ሳታሰማ ምንም ማድረግ አይገባህም” አሉት፡፡ አቡነ ቄርሎስ ይህን ማለታቸው በዲፕሎማቲክ ደረጃ ለዓለም ለማሰማት እና የአቡነ ጴጥሮስን ህይወት ለማትረፍ አስበው እንደነበር ግልጽ ነው፡፡ ነገር ግን ግራዚያኒ ይህ የአቡነ ጴጥሮስ የሞት ፍርድ እንኳንስ እስከ ግብፅ ከአዲስ አበባ ውጪ እንኳን ከመሰማቱ በፊት በግማሽ ቀን እንዲፈፀም ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ በእርግጥ ምንም እንኳን ከመገደል ባያመልጡም ብፁዕነታቸው እንደተያዙ ንቡረ ዕድ ተክለሀይማኖት/አዲስ ተክሌ/ና ሌሎች ሊቃውንት ወደ አቡነ ጴጥሮስ ዘንድ በመሄድ ማልደዋቸው ነበር ይባላል፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቁመታቸው ረዘም፣ ፊታቸው ዘለግ ያለ፣ መልካቸው ጠየም ያለ፣ አዋቂነታቸው እና ትህትናቸው ከገፃቸው የሚነበብ ሲሆን በዚህ ጊዜ ለብሰውት የነበረው ልብስ ጵጵስና ጥቁር ካባ ያውም በጭቃ የተበከለ ነበር ፡፡ በዚህ ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ችሎት ቀረቡ፡፡ ለፍርድም የተሰየሙት ዳኞች ሦስት ሲሆኑ እነዚህም የጣሊያኖች የጦር ሹማምንት ናቸው፡፡ የመካከለኛው ዳኛ ኮሎኔል ነበር፡፡ የቀረበባቸውም ወንጀል ሕዝብ ቀስቅሰዋል፣ እራስዎም ዐምፀዋል፣ ሌሎችንም እንዲያምፁ አድርገዋል የሚል ነበር፡፡ ዳኛውም “ካህናቱም ሆኑ የቤተ-ክህነት ባለሥልጣኖች ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የኢጣሊያንን መንግሥት ገዢነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን ዐመፁ? ለምን ብቻዋን አፈንጋጭ ሆኑ?” ሲል ጠየቃቸው፡፡ አቡነ ጴጥሮስም የሚከተለውን መለሱ፡፡ “አቡነ ቄርሎስ ግብፃዊ ናቸው፤ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡ ሐላፊነትም ያለብኝ የቤተ ክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡ ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም፡፡ ለፈጣሪዬ ብቻ የምናገረውን እናገራለሁ፡፡ እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ ዐውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ” አሉ፡፡ “ይህንንም ብለው በጥይት ተደብድበው ሲገደሉ እንዲያይ ተጋብዞ ለተሰበሰበው ሕዝብ የሚከተለውን ሕያው መልእክት አስተላለፉ “አረማዊ የሆነው የፋሺስት መንግሥት ቤተ-ክርስቲያንን ለማቃጠል፣ ሕዝበ ክርስቲያንን ለመግደል፣ ሃይማኖትን ለማጥፋት፣ ታሪካችንን ለማበላሸት የመጣ ነው እንጂ በጎ ለመሥራት እውነተኛ ፍርድ ለመስጠት ስላልመጣ ለዚህ ለግፈኛ አትገዙ፡፡ ስለ ውድ ሀገራችሁ፣ ስለ ቀናች ሃይማኖታችሁ ተከላከሉ፡፡ ነፃነታችሁ ከሚረክስ ሙታችሁ ስማችሁ ቢቀደስ ታላቅ ዋጋ ያለው ክብር ታገኛላችሁ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዚህ ለጠላት እንዳይገዛ አውግዣለሁ፤ የኢትዮጵያ መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች ትሁን፡፡ በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተገዘተች ትሁን፡፡” ጋዜጠኛው ይቀጥላል፡፡ “እኒህ ጳጳስ ሐቀኛ ነበሩ፡፡ ነገር ግን ለኢጣሊያ ለጋስዮን ታዝዞ የመጣው አስተርጓሚ ዳኞች የሚሉትን ብቻ ከማስተርጎም በቀር ጳጳሱ የሚናገሩትን ሐቀኛ ንግግር አላስተረጎመም፡፡ እኔ እንኳን የሰማሁት በአዲስ አበባ ለሠላሳ ዓመት የኖረው የእቴጌ ሆቴል ሐላፊ የነበረው የግሪክ ዜጋ ማንድራኮስ አጠገቤ ተቀምጦ ስለ ነበር የተናገሩትን ሁሉ ስለ ገለጠልኝ ነው፡፡ እኔ እንደ ሰማሁት ፍርዱን ለመስማት በብዛት የተሰበሰቡት ጣሊያኖችና ታዝዞ የወጣው የአዲስ አበባ ሕዝብ ሐቀኛ የሆነውን ንግግራቸውን ቢሰሙ ኖሮ ልባቸው ይነካ ነበር” ይላል፡፡ ሆኖም አስተርጓሚው በጳጳሱ ላይ ተፅዕኖ ስላሳደረባቸው እውነተኛ ንግግራቸው ሳይገለጥ ቀረ፡፡ ቀጥሎም ብፁዕነታቸው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለ ርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየፀለዩ ሕዝቡን ባረኩ ፡፡ ወዲያው የሞታቸው ፍርድ ሲሰማ ሕዝቡ በኢጣልያ የእጅ ሰላምታ ዓይነት እጁን እንዲያነሳ ታዘዘ ፡፡ በዚያን ጊዜ አቡነ ጴጥሮስ የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ ፡፡ ሰዓቱም 5፡15 ነበር ፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉ ምንም ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር፡፡ የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣሊያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥ ነበር ፡፡ ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ላይ ይታይ ነበር፡፡ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፳፰ ፤ ፭፡፲፭ ሰዓት ይሙት በቃ የተፈረደባቸው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉና ደክሞአቸው ስለነበር ለመቀመጥ ፈልገው ዳኛውን በትሕትናና በፈገግታ ጠየቁት ፡፡ እንዲቀመጡም ፈቀደላቸው ፡፡ በመጨረሻም የሞታቸው ፍርድ ከተነበበ በኋላ የፈረዱባቸውን ዳኞች ጸልየው በመስቀላቸው ባረኩዋቸው ፡፡ ብፁዕነታቸው እስከ መቃብር አፋፍ ድረስ የፍርሃትና የድንጋጤ ምልክት ያይደለ ከልብ የሆነ ፍጹም ቆራጥነት ይታይባቸው ነበር፡፡ የሀገራቸው በጠላት መወረር፣ የሕዝባቸው መገደልና መታሰር፣ የቤተ ክርስቲያናቸው መደፈር እስከ ሞት ያደረሳቸው እኒህ እውነተኛ ጳጳስ ለመገደል ሲወሰዱ ጥይት አልፎ ሌላ ሰው እንዳይጎዳ ግንብ ይፈለግ ጀመር፡፡ ሩቅ ባለመሔድ ከመካነ ፍትሑ 10 ሜትር ርቆ ግንብ ያለው መግደያ ቦታ ተገኘና ወደዚያ ተወሰዱ ፡፡ ከገዳዮቹም አንዱ “ፊትዎን ለመሸፈን ይፈልጋሉን?” ሲል ጠየቃቸው ፡፡ “ይህ የአንተ ሥራ ነው” ሲሉ ብፁዕነታቸው መለሱ ፡፡ ከመግደያውም ቦታ እንደደረሱ ወንበር ቀረበላቸውና ፊታቸውን ወደ ግንቡ ጀርባቸውን ወደ ሕዝቡ አድርገው እንዲቀመጡ ሆኑ ፡፡ ከዚያ በኋላ ስምንት ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ ርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተጠንቀቅ ቆሙ ፡፡ ወዲያው አዛዡ “ተኩስ” በማለት ትእዛዝ ሲሰጥ ስምንቱም ተኩሰው መቱዋቸው ፡፡ ግን በስምንት ጥይት ሳይሞቱ ቀሩ ፡፡ መሞታቸውንና አለመሞታቸውን ለማረጋገጥ ዶክተር ተጠራ ፡፡ ዶክተሩም እንዳልሞቱ አረጋገጠ ፡፡ ከዚያም ሌላ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገደላቸው ፡፡ ብፁዕነታቸው የተገደሉበት ቦታ መኻል አዲስ አበባ ዛሬ መታሰቢያ ሐውልታቸው ቆሞ በሚገኝበት ቦታ አካባቢ ነው፡፡ “የብፁዕነታቸው አስክሬን ማንም እንዳይወስደው በአስቸኳይ ከአዲስ አበባ ውጭ ማንም በማያውቀው ቦታ በምሥጢር እንዲቀበር ተደረገ ፡፡ በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ ፡፡” ይህ ጋዜጠኛ የሰጠው ምስክርነት የብፁዕ አባታችን አቡነ ጴጥሮስን የመሪ ሀገር ወዳድነትና የኢትዮጵያን ሕዝብ ታጋሽነትና ጀግንነት ሲያረጋግጥ ይኖራል ፡፡ የብፁዕነታቸውን በድን በተመለከተ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያናችን አባቶች ቅዱሳን መላእክት የጻድቃንን በድን እያመጡ እንደሚያስቀምጡበትና በውስጡ የሚቀመጥ አስክሬን እንደማይፈርስ ወደሚነገርለት አቡነ መልከ ፄዴቅ ዋሻ /ሰሜን ሸዋ/ መላእክት ወስደው እንዳስቀመጡትና በዚያ እንደታዬ ይናገራሉ ፡፡ በተጨማሪም ደራሲና ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ “አቡነ ጴጥሮስ እንዴት ሞቱ?” ሲል ሙሴ ፓይላክን ጠይቋቸው እርሳቸውም የሚከተለውን ተናግረዋል ፡፡ “አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ ፡፡ መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት ፡፡ ቀጥለውም በያዙት መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ ፡፡ የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከኪሳቸው ከተቱት ፡፡ ወዲያው ወታደሮች በሩምታ ተኩሰው ገደሉዋቸው ፡፡ ይህ እንደ ሆነ አስገዳዩ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ ፡፡ ማታ ከአስገዳዩ ኮሎኔል ጋር ተገናኝተን ስንጫወት: “በዚህ ቄስ መገደል እኮ ሕዝቡ ተደስቷል” አለኝ፡፡ “እንዴት?” ብለው “አላየህም ሲያጨበጭብ” አለኝ ፡፡ እኔም “ባታውቀው ነው እንጂ የሕዝቡ ባሕል ሲናደድም ያጨበጭባል” አልኩት ፡፡ “እንዴት?” ቢለኝ እጄን እያጨበጨብኩ አሳየሁት ፡፡ እሱም አሳየኝ ፡፡ “ከዚህ በኋላ የሆነው ቢሆን እኔ ትልቅ ማስታወሻ አግኝቼአለሁ” ብሎ አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ ይዘውት የነበረውን መስቀልና መጽሐፍ ቅዱስ ፣ የኪስ ሰዓታቸውን ጭምር አሳየኝ ፡፡ መጽሐፍ ቅዱሱ መሐል ለመሐል በጥይት ተሰንጥቋል ፡፡ መስቀሉም ልክ በመሐከሉ ላይ ጥይት በስቶት ወጥቷል፡፡ የኪስ ሰዓታቸውንም እንዳየሁት እንደዚሁ ጥይት በስቶታል” ብለው ያዩትን መስክረዋል ፡፡ የመታሰቢያ ሐውልት የብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ጥብአት ማለትም ለሀገራቸውና ለእምነታቸው እስከ መጨረሻዋ ሰዓት ድረስ መስክሮ ማለፍ ምክንያቱ በልጅነታቸው ከቅኔ መምህራቸው የሰሙት የአደራ ቃል እንደሆነ ይነገራል፡፡ አለቃ ተጠምቀ የተባሉ ቅድስናን ከሊቅነት አስተባብረው የያዙ መምህራቸው አንድ ቀን ብፁዕነታቸውን ጠርተው “ኃይለ ማርያም፣ አንተ ወደ ፊት ጳጳስ ትሆናለህ፡፡ በዚያ ጊዜ አረመኔ በዚህች ሀገር ይሠለጥናል፡፡ ታዲያ ያኔ አንተ ለነፍስህ ሳትሰቀቅ በሰማዕትነት እለፍ፡፡ ሰማዕትነት ክፍልህ ነው፡፡ አደራ” ብለዋቸው ነበር ይባላል፡፡ ይህንን የመምህራቸውን የአደራ ቃል የያዙት ብፁዕነታቸው እስከ መጨረሻው ለነፍሳቸው ሳይፈሩ፣ አንዲትም ቀን ሳይሸሹ ከላይ በቀረበው ሁኔታ የሰማዕትነት ጽዋቸውን ሊቀበሉ ችለዋል፡፡ ጠላት ድል ተደርጎ ሀገራችን ነፃነቷን ከተቀዳጀት በኋላ የብፁዕነታቸውን አኩሪ ታሪክ ትውልድ ሲያዘክርላቸው እንዲኖር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት አሳሳቢነት ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ሐውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ከድል በኋላ የብፁዕነታቸው ሐውልት ተመርቆ የቤተ መንግሥቱም ሆኑ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት አበባ ጉንጉን ከሐውልቱ ሥር ሲያስቀምጡ ከቤተ ክህነት ካስቀመጡት አባቶች አንዱ በ1921 ዓ.ም አብረዋቸው የተሾሙት ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ነበሩ፡፡ ትውልድ ሁሉ ለሀገር ክብርና ለነጻነት በተከፈለው፡፡ የብዕፁነታቸው ሕይወት እንዲማርበትና ሕያው ምስክር ሆኖ እንዲኖር የቆመላቸውን ሐውልት ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በክብር ይጠብቁታል ፡፡ '''''የእኝህን ታላቅና ቅዱስ ሰማዕት አባት ክብርና ተጋድሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከአምስት ዓመት በፊት ቅዱስ /ሰማዕት/ ብሎ በማጽደቅ በስማቸው በቅድስና ማዕረግን ሰጥቶ በስማቸው ታቦት ተቀርጾ ቤተክርስቲያን እንዲሰራላቸው ወስኗል ፡፡ ይህም በተወለዱበት በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሃገረሰብከት በፍቼ ከተማ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ አርበኛ፣ ጀግና፣ ጳጳስ፣ ሰማዕት ቅዱስም የሆኑ አባት ናቸው ፡፡'''''
50825
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B0%E1%89%A3%E1%8A%A0%E1%8B%8A%20%E1%88%98%E1%89%A5%E1%89%B6%E1%89%BD
ሰባአዊ መብቶች
አለም አቀፍ የሰብእዊ መብቶች ድንጋጌ • የመላውን የሰው ዘር ተፈጥሮእዊ ክብር እንዲሁም የማይገሰሱ እና እኩል የሆኑ መብቶች ማክበርና እውቅና መስጠት ለዓላማችን ሰላም ፍትህና ነጻነት ዋና መሰረት በመሆኑ፤ • የሰብእዊ መብቶች ጥሰትና አለመከበር አሰቃቂ ለሆኑና ለህሊናም ዘግናኝ ለሆኑ ተግባራት መንሰኤ ሆኖአል። ይህንንም ተከትሎ ሁሉም የሰው ልጆች የንግግርና የዕምነት ነጻነቶችን በሚቀዳጁበት እንዲሁም ከፍርሃት ነጻ ሆነው የሚኖሩበት የአለም አኗኗር ስርእት አሙን መሆን የአያንዳንዱ ሰው ተቀዳሚ ምኞት በመሆኑ፤ • የሰው ልጅ አምባገነናዊነትንና ጭቆናን ለማስወገድ አመጽን እንደ እማራጭ እንዳይወስድ ሰብእዊ መብቶች በህግ የበላይነት መጠበቅ ስለሚገባቸው፤ 1. በሃገራትም መካከል መልካም ግንኙነቶችን ማዳበርና ማሳደግ አስፈላጊ በመሆኑ፤ • የተባበሩት መንግስታት አባል ሀገራት በመሰረታዊ ሰብእዊ መብቶች፤ በሰው ልጅ ክብርና ዋጋ፤ በወንዶችና በሴቶች የአኩልነት መብቶች እንዲሁም በማህበራዊ መሻሻልና የኑሮ ደረጃ አድገት ላይ ያላቸውን ጽኑ እምነት በጋራ መተዳደሪያ ሰነዳቸው ላይ • አባል ሃገራት በራሳቸውና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ለሰብእዊ መብቶችና መሰረታዊ ነጻነቶች መከበርና መስፋፋት ዕውን መሆን ቃል ኪዳን በመግባታቸው፤ • በነዚህ መብቶችና ነጻነቶች ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ መፍጠሩ ለቃል ኪዳኑ ገሃዳዊ ተግበራዊነት ከፍተኛ ጠቀሜታ አና አስተዋጽኦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ይህንን እለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ እያንዳንዱ ግለሰብ እና የማህበረሰብ አካል እነዚህን መብቶችና ነጻነቶች ለማስከበር፤ በዕለት ተዕለት በማስታወስ በማስተማርና በማስገንዘብ እንዲሁም ሀገር አቀፍና አለም አቀፍ ሂደታዊ አርምጃዎችን በመውሰድ የስኬታማነት የጋራ መስፈርት ሆኖ የተቀመጠውን የሰብእዊ መብቶችና ነጻነቶች ውጤታማ አለም አቀፋዊ እውቅናና መከበር በአባል ሃገራት ህዝቦችና በመላው አስተዳደራዊ ግዛቶቻቸው ይሰፍን ዘንድ ይህንን አዋጅ አንቀጽ 1 የሰው ልጅ በተፈጥሮው ነፃ ነው። በክብርና በመብትም አኩል ነው። የሚያስተውል ህሊናም በተፈጥሮ የተለገሰ በመሆኑ አንዱ ከሌላው ጋር በወንድማማችነት መንፈስ ሊኖር ይገባዋል :: አንቀጽ 2፤ ሁሉም ሰው በዚህ ድንጋጌ ውስጥ የሰፈሩትን ሁሉንም መብቶችና ነፃነቶች ያለምንም ዓይነት የዘር የቀለም የፆታ የቋንቋ የሃይማኖት የፖለቲካ ወይም ሌላ አይነት አስተሳሰብ የብሄራዊ ወይም ማህበራዊ ታሪክ የሃብት የትውልድ ወይም ሌላ አይነት ሁኔታዎች ልዩነት ሳይደረግበት የመጠቀም መብት አለው:: አንቀጽ 3፤ ሁሉም ሰው በነፃነትና በሰላም የመኖር መብት አለው:: አንቀጽ 4፤ ማንም ሰው በባርነትና በባርነት ቀንበር መያዝ የለበትም ባርነትና የባሪያ ንግድ በማንኛውም መልኩ የተከለከለ ነው:: አንቀጽ 5 ማንም ሰው በስቃይ ወይም በጭካኔ እንዲሁም ኢሰብአዊና ክብረ ነክ ወይም አዋራጅ በሆነ አያያዝ መያዝ ወይም መቀጣት የለበትም :: አንቀጽ 6 ሁሉም ሰው በየትኛውም ቦታ በህግ ፊት እንደሰው የመታየት መብት አለው:: አንቀጽ 7 ሁሉም ሰዎች በህግ ፊት እኩል ናቸው ሁሉም ሰዎች ያለምንም ልዩነት እኩል የሆነ ህጋዊ ከለላ እና ጥበቃ የማግኘት መብት አንቀጽ 8 እያንዳንዱ ሰው በህግ ወይም በህገ መንግስት የተሰጡት መሰረታዊ መብቶች ላይ ጥሰት በሚደርስበት ጊዜ ችሎታ ባላቸው ብሄራዊ የፍትህ ተቋማት ውጤታማ የሆነ ፍትህ የማግኘት መብቱ የተጠበቀ ነው :: አንቀጽ 9 ማንም ሰው ያለፍርድ በግዞት መያዝ ወይም መታሰር የለበትም :: አንቀጽ 10 እያንዳንዱ ሰው በመብቶቹ ና በግዴታዎቹ አፈፃፀም እንዲሁም በሚከሰስበት ማንኛውም አይነት የወንጀል ክስ ጉዳዩ ነፃ በሆነና በማያዳላ እንዲሁም ትክክለኛና ፍታዊ በሆነ የፍርድ ሸንጎ እንዲታይለት የማድረግ ሙሉ መብት አለው:: አንቀጽ 11 1. በወንጀል ክስ የተከሰሰ ማንኛውም ሰው ለመከላከያው አስፈላጊ የሆኑትን ሁሉ አቅርቦ በሚከራከርበት የይፋ የፍርድ ሸንጎ ወይም ችሎት ወንጀለኛ መሆኑ በህግ እስከሚረጋገጥበት ድረስ ከወንጀል ነፃ እንደሆነ የመቆጠር መብት አለው:: 2.ማንም ሰው በብሄራዊ ወይም አለምዓቀፍ ህግ መሰረት ወንጀል ሆኖ ያልተደነገገን ተግባር በመፈፀሙ በጊዜው ወንጀለኛ ተብሎ ሊከሰስ አይችልም እንዲሁም ወንጀሉ በተፈፅመበት ጊዜ ከተደነገገው ቅጣት ይበልጥ አይፈረድበትም:: አንቀጽ 12 ማንም ሰው በግል ኑሮው በቤተሰቡ በቤቱ ውስጥ ወይም በሚፃፃፈው ደብዳቤ ላይ ከፍርድ ውጭ ከሚደረግ ጣልቃገብነት ነፃ ነው:: እንዲሁም ክብርና ዝናን ከሚነኩት ማንኝቸውም አይነት ጥቃቶች የተጠበቀ ነው:: እያንዳንዱ ሰው እነዚህን ከመሰሉ ጣልቃ ገብነትና ጥቃቶች ህጋዊ ከለላ የማግኘት መብት አለው:: አንቀጽ 13 1 እያንዳንዱ ሰው በሃገሩውስጥ ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስና የመኖር መብት አለው:: 2 እያንዳንዱ ሰው የራሱን ወይም የየትኛውንም አገር ለቆ የመሄድ እንዲሁም ወደራሱም አገር የመመለስ መብት አለው:: አንቀጽ 14 1 እያንዳንዱ ሰው ከጭቆና ሸሽቶ በሌሎች ዓገሮች ጥገኝነት የመጠየቅና በደህና የመኖር መብት አለው :: 2 ፖለቲካዊ ካልሆኑ ወንጀሎች ወይም የተባብሩት መንግስታት ድርጅትን ዋና ዓላማዎችን ከሚቃረኑ ስራዎች የተነሳ በሚደርሱ ክሶች ምክንያት ከሆነ ይህ መብት ሊያገለግል አይችልም:: አንቀጽ 15 1 ሁሉም ሰው የዜግነት መብት አለው :: 2 ማንም ሰው ያለፍርድ ዜግነቱ አይወሰድበትም ወይም ዜግነቱን የመለወጥ መብት አይነፍገውም:: አንቀጽ 16 1 ለአካለ መጠን የደረሱ ወንዶችና ሴቶች በዘር በብሄርና በሃይማኖት ልዩነት ሳይወሰኑ ጋብቻን የመፈፀምና ቤተሰብን የመመስረት መብት አላቸው።ጋብቻ በመፈጸም በት ጊዜና ጋብቻ በሚፈርስበትም ጊዜ እኩል መብት አላቸው :: 2 ጋብቻ የሚፈፀመው ሁለቱም ተጋቢዎች በሚያደርጉት ነፃና ሙሉ ስምምነት መሰረት ብቻ ነው:: 3 ቤተሰብ የማህበረሰብ ተፈጥሮአዊና መሰረታዊ ክፍል በመሆኑ በህብረተሰቡና በመንግስት ጥበቃ ሊደረግለት ይገባል :: አንቀጽ 17 1 ሁሉም ሰው በግል ወይም በጋራ ንብረት የማፍራትና የንብረት ባለቤት የመሆን መብት አለው :: 2 ማንም ሰው ያለፍርድ ንብረቱን ሊነጠቅ አይችልም :: አንቀጽ 18 ሁሉም ሰው የሃሳብ የህሊናና የሀይማኖት ነፃነት መብት አለው:: ይህም መብት ሀይማኖቱን ወይም እምነቱን የመለወጥ ነፃነትንና ብቻውን ወይም ከሌሎች ጋር ሆኖ በይፋ የማስተማር በተግባር የመግለፅ የማምለክና የማክበር ነፃነትን ይጨምራል:: አንቀጽ 19 ሁሉም ሰው የሀሳብና ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት አለው :: ይህ መብት ሀሳብንና መረጃን ያለምንም ገደብ የማግኘትን የመቀበልን የማካፈልንና ያለምንም ጣልቃ ገብነት በሀሳብ የመፅናትን ያጠቃልላል:: አንቀጽ 20 1 ሁሉም ሰው በሰላማዊ መንገድ የመሰብሰብና የመደራጀት መብት አለው:: 2 ማንም ሰው የየትኛውም ማህበር አባል እንዲሆን ሊገደድ አይችልም:: አንቀጽ 21 1 ሁሉም ሰው በሀገሩ የመንግስት አስትዳደር ውስጥ በቀጥታ ወይም ነፃ በሆነ ሂደት በተመረጡ ተወካዮች አማካኝነት ተሳትፎ የማድረግ መብት አለው :: 2 ሁሉም ሰው የሀገሩን ህዝባዊ አገልግሎቶች የመጠቀም እኩል የሆነ መብት አለው:: 3 የመንግስት ስልጣን በህዝብ ፍላጎጎትና ስምምነት ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት:: ይህም የህዝብ ፍላጎተና ስምምነት አለም አቀፍና ለሁሉም እኩል ቢሆን እንዲሁም በምስጢር በሚደረግ የድምፅ መስጠት ምርጫ ወይም ተመጣጣኝ በሆነ ድምፅን የመግለፅ ሁኔታ በየጊዜውና በትክክል በሚፈፀሙ ምርጫዎች የሚረጋገጥ መሆን አለበት:: አንቀጽ 22 እያንዳንዱ ሰው የህብረተሰብ አካል እንደመሆኑ መጠን ማህበራዊ ደህንነቱ የመጠበቅ መብት አለው:: በተጨማሪም በብሄራዊና አለም አቀፍ ጥረትና ትብብር እንዲሁም በመንግስታዊ ድርጅቶችና የሀብት ምንጬች ለክብሩና ለሰብዓዊ ነፃ እድገቱ አስፈላጊ የሆኑ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና የባህል መብቶች በተግባር እንዲረጋገጡለት የመጠየቅ መብት አለው:: አንቀጽ 23 1 ሁሉም ሰው ስራ የመስራትና ከስራ አጥነት የመጠበቅ መብት አለው:: እንዲሁም ነፃ የስራ ምርጫና ፍትሀዊና ተስማሚ የሆነ የስራ ሁኔታ የማግኘት መብት አለው:: 2 ሁሉም ሰው ያለምንም አድልዎ ለተመሳሳይ ስራ ተመሳሳይ ክፍያ የማግኘት መብት አለው :: 3 በስራ ላ ይ ያለ ሰው ለራሱና ለቤተሰቡ ሰብአዊ ክብር ተገቢ ደህንነት መጠበቂያ ዘዴዎች የተደገፈ ትክክለኛና ተስማሚ ዋጋን የማግኘት መብት አለው :: 4 እያንዳንዱ ሰው ጥቅሞቹን ለማስከበር የሙያ ማህበሮችን የማቋቋምና አባልም የመሆን መብት አለው :: አንቀጽ 24 እያንዳንዱ ሰው እረፍት የማግኘትና የመዝናናት መብት አለው እንዲሁም በአግባብ የተወሰኑ የስራ ሰዓቶችና በየጊዜው የእረፍት ጊዜያትን ከደሞዝ ጋር የማግኘት መብት አለው :: አንቀጽ 25 1 እያንዳንዱ ሰው ለእራሱና ለቤተሰቡ ጤንነትና ደህንነት ምግብ ልብስ ቤትና ህክምና አስፍላጊ የማህበራዊ ኑሮ አገልግሎቶችም ጭምር የሚበቃ የኑሮ ደረጃ ለማግኘት መብት አለው :: ስራ ሳይቀጠር ቢቀር ቢታመም ለመስራት ባይችል ባል ወይም ሚስት ቢሞት ቢያረጅ ወይም ከቁጥጥሩ ውጭ በሆኑ ምክንያቶች መሰናክል ቢገጥመው ደህንነቱ እንዲጠበቅለት መብት አለው:: 2 ወላድነትና ህፃንነት ልዩ ጥንቃቄና እርዳታ የማግኘት መብት አላቸው :: በጋብቻ ወይም ያለጋብቻ የሚወለዱ ህፃናትም በተመሳሳይ ደህንነታቸው የመጠበቅ መብት አላቸው:: አንቀጽ 26 1.እያንዳንዱ ሰው የመማር መብት አለው። ትምህርት ቢያንስ ቢያንስ በመሰረታዊና በአንደኛ ደረጃ በነፃ መቅረብ ይገባዋል:: የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መማር ግዴታ ነው:: የቴክኒክና የልዩ ልዩ ሙያ ትምህርት በጠቅላላው የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ደግሞ በችሎታ መሰረት ለሁሉም እኩል መቅረብ አለበት :: 2.ትምህርት ለእያንዳነዱ ሰው ሁኔታ ማሻሻያና ለሰብአዊ መብቶችም እንዲሁም ለመሰረታዊ ነፃነቶች ክብር ማዳበርያ የሚውል መሆን አለበት:: እንዲሁም የተለያየ ዘር ወይም ሀይማኖት ባሏቸው ህዝቦች መካከል ሁሉ መግባባትን ተቻችሎ የመኖርንና የመተባበርን መንፈስ የሚያጠናክርና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰላምን ለመጠበቅ የሚፈፅማቸው ተግባራት እንዲስፋፋ የሚደረግ እና የሚያበረታታ መሆን አለበት :: 3.ወላጆች ለልጆቻቸው ለመሰጠት የሚፈልጉትን ትምህርት ለመምረጥ ቅድሚያ መብት አላቸው :: አንቀጽ 27 1 እያንዳንዱ ሰው በህብረተሰቡ የባህል ሕይወት በነፃ መካፈልና በኪነ ጥበብ ለመጠቀም በሳይንስ እርምጃና በጥቅሞቹም ለመሳተፍ መብት አለው:: 2 እያንዳንዱ ሰው ከደረሰው ማንኛውም የሳይንስ የድርሰትና የኪነጥበብ ስራ የሚያገኘው የሞራልና የሀብት ጥቅሞች እንዲከበሩለት መብት አለው :: አንቀጽ 28 ሁሉም ሰው በዚህ ድንጋጌ ውስጥ የሰፈሩት መብቶችና ነፃነቶች ሙሉ በሙሉ በተገባር ሊውሉ የሚችሉበት ማህበራዊና አለም አቀፋዊ የኑሮ ስርአት አባል የመሆን መብቱ የተጠበቀ ነው :: አንቀጽ 29 1 እያንዳንዱ ሰው ለስብእናው ነፃና ሙሉ እድገት ብቸኛ መሰረት ለሆነው ለሚኖርበት ማህበረሰብ ሊፈፅማቸው የሚገቡ ግዴታዎች አሉት:: 2 እያንዳንዱ ሰው በመብቶቹና በንፃነቶቹ በሚጠቀምበት ጊዜ ገደብ የሚያ ጋጥመው የዴሞክራሲያዊ ማህበረሰብ መሰረታዊ መስፈርቶች የሆኑትን ግብረገብነትን ስርዓተ ማህበርና የጋራ ደሀንነትን ለማረጋገጥ እና የሌሎችን መብቶችና ነፃነቶች ለማሳወቅና ለማክበር በህግ የተቀመጡ ገደቦችን እንዳይተላለፍ ብቻ ነው :: 3 እነዚህ መበቶችና ነፃነቶች በማንኛውም ሁኔታ የተባበሩት መንግስትታት መሰረታዊ አላማዎች በሚቃረን መንገድ ሊፈፀሙ አይገባቸውም :: አንቀጽ 30 በዚህ ውሳኔ ላይ የተዘረዘረውን ሁሉ በዚሁ ውስጥ የተጠቀሱትን ማናቸውንም መብቶች ወይም ነፃነቶች የመጣስ ድርጊትን ለመፈፀም ለማንኛውም መንግስት ወይም ድርጅት ወይም ሰው የተከለከለ ነው ::
17527
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%89%A5%E1%88%A8%20%E1%88%8A%E1%89%A3%E1%8A%96%E1%88%B5
ደብረ ሊባኖስ
ደብረ ሊባኖስ በጥንቱ ግራርያ አውራጃ (በአሁን ስሙ ሰላሌ ) ሸዋ የሚገኝ ጥንታዊ ገዳም ነው። ገዳሙ በመጀመሪያ ደብረ አስቦ ሲባል የአሁን ስሙን የያዘው በአጼዘርዓ ያዕቆብ አነሳሽነት በ፲፬፴፯ ዓ.ም ነው። ስለገዳሙ ምሥረታ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገድል መሠረት፣ ይህ ገዳም የተመሰረተው በ1300ዎቹ መጀመሪያ በራሳቸው በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ነበር። ተክለ ሃይማኖት የግራርያን ስዩም የነበረውን ሰሜን ሰገድን ክርስትና እንዲቀበል ካደረጉ በኋላ፣ ይሄው ሹም ለተክለ ሃይማኖት አስቦ ከተባለው ስፍራ መሬት ለክርስትና ግልጋሎት በፈቃድ ስለሰጠ፣ በዚሁ ቦታ ለቅድስት ማሪያም መታወሻ የሚሆን ቤ/ክርስቲያን ተቋቋመ። ይህ በንዲህ እንዳለ በ15ኛው ክፍለ ዘመን የቤ/ክርስቲያኑ ቄስ ገበዝ ቴዎድሮስ ለራሳቸው ለጻዲቁ አቡነት ተክለ ሃይማኖት መታሰቢያ የሚሆን ቤ/ክርስቲያን አስገነቡ። ይህ ቤ/ክርስቲያን እስከ ተገነባ ድረስ ቀሳውስቱ በአካባቢው ዋሻወች ይኖሩ እንደነበር ትውፊት አለ። ከ15ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ የደብረ ሊባኖስ መሪዎች በእጨጌ ማዕረግ የአጠቃላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን ገዳም ስርዓት መሪ ሆኑ። ከ1437 ጀምሮ አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ለገዳሙ አዲስ ስም በማውጣት ደብረሊባኖስ ካሉት በኋላ፣ ለቤተ ክርስቲያኑ መሬትን በመስጠት ገዳሙ እራሱን እንዲችል አድርገዋል በዚሁ በ15ኛው ክፍለ ዘመን አዳዲስ መጻህፍት በደብሩ ታተሙ። ከነዚህ ውስጥ ገድለ ተክለ ሃይማኖት፣ ገድል ፊልጶስና መጽሐፈ ፍልሰቱ ለተክለ ሃይማኖት ይገኙበታል። ስለ ገዳሙ ማህበረ ሰብ ምንም እንኳ በ1524ዓ.ም. ይህ ገዳም በግራኝ አህመድ ቢፈርስም፣ የገዳሙ ማህበራዊ ስርዓት ግን ሳይፈረስ ቀጥሏል። ሆኖም በጊዜው የነበሩት የደብረ ሊባኖሱ እጨጌ ዮሐንስ ከአጼ ገላውዲዎስ ጋር ኑር ሙጋህድን ሲዋጉ፣ 1551ዓ.ም. ላይ አረፉ። ከዚህ በኋላ አጼ ሠርፀ ድንግል ገዳሙን የአገሪቱ የሃይማኖት ማዕከል ለማድረግ ቢሞክሩም ኋላ ላይ የብዙ ኦሮሞ ቡድኖች አካባቢውን ስለወረሩትና ከተቀረው የአገሪቱ ክፍል ስለተለያየ ሳይሳካ ቀረ። በእጨጌ ዘረ ወንጌልና እጨጌ አብርሃም ዘመን የደብረ ሊባኖስ ማህበረሰብ ጓዙን በመጠቀለል ወደ ጣና ሃይቅ፣ እንፍራዝተሰደደ። በዚህ መሰረት ቤተ ተክለ ሃይማኖት፣ በአዘዞ፣ ጎንደር ተቋቋመ። ይሄውም በአሁኑ ዘመን አዘዞ ተክለ ሃይማኖት የሚባለው ነው። ይህ ማህበረሰብ በ18ኛው ክፍለ ዘመን ግራርያ ላይ ጉብኝት በማድረግ የደብረ ሊባኖስን ገዳም እንደገና ከማቋቋሙም በላይ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን መቃብር ለማግኘት ችሏል። ስለ ገዳሙ ሕንፃ የገዳሙን ዋና ሕንፃ ከኢትዮጵያ ነገሥታት ብዙዎቹ ያማረ በመሰላቸው፤ ጊዜያቸው በፈቀደላቸው ጥበብ ሕንፃውን አሠርተዋል። ለምሳሌ፤ የመጀመሪያውን ሕንፃ ያሳነፁት በ፲፪፻፷ የነገሡት አጼ ይኩኖ አምላክ ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ በ፲፬፻፭ ዓ/ም የነገሡት አጼ ይስሐቅ ነበሩ። እንዲሁም በ፲፰፻፬ ዓ/ም በወሰን ሰገድ፣ በ፲፰፻፸፮ ዓ/ም አጼ ዮሐንስ፣ በ፲፱፻ ዓ/ም በዳግማዊ ምኒልክ እንደገና ታንጿል። የሥፍራው ገደላማ አቀማመጥ እና የአፈሩ የመሸሽ ባህሪ ለሕንጻው የማይስማማ በመሆኑ ግንቡ ለብዙ ጊዜ ሊያገለግል አልቻለም። በመጨረሻ፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን፣ ከጥልቅ የግንባታ ጥናት በኋላ ተሠርቶ ኅዳር ፱ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ/ም ቅዳሴ ቤቱ ተመረቀ። የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቃል ኪዳን ንጉሠ ነገሥቱ የጣልያንን ጦር ለመግጠም በደሴ በኩል ወደማይጨው ሲዘምቱ፤ እግረ መንገዳቸውን ገዳሙን ለመጎብኘት ኅዳር ፲፮ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም ሄደው ለእጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ (በኋላ አቡነ ባስልዮስ) ወንጌል ላይ “በገንዘብ የማትገዛ አምላክ መሆንህን አምናለሁ፤ ያንተ ያልሆነ የለኝምና…” የሚል ቃል ጽፈው ሰጧቸው። ፋሺስት ኢጣሊያ ድሉን ከተቀዳጀች በኋላ በጨካኙ ማርሻል ግራዚያኒ ትዕዛዝ በ፲፱፻፳፱ ዓ/ም የገዳሙ የገዳሙ መነኮሳት ሲጨፈጨፉና ገዳሙም ተበዝብዞ ሲቃጠል፤ ይሄ ወንጌል ከሌላ ንብረት ጋር ተዘርፎ ከሰው ወደሰው ሲዘዋወር ቆይቶ በመጨረሻ አቡነ አብርሃም እጅ እንደገባ እና እሳቸውም በምስጢር ጠብቀው አቆይተው በሚያርፉበት ጊዜ ለሚወዷቸው የመንፈሳዊ ልጃቸው ለመምህር ሰይፈ ሥላሴ “ይኸን የንጉሠ ነገሥቱ የብፅዓት ቃል ያለበትን መጽሐፍ፤ መምጣታቸው አይቀርምና እንደገቡ አስረክብልኝ” ብለው አደራ ሰጥተው እንዳረፉ ተዘግቧል። ቤተ ክርስቲያኑም ለብዙ ጊዜ ተዘግቶ ነበር። መምህር ሰይፈ ሥላሴም ከጠላት ወረራ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ተመልሰው ወደ ከጎጃም ወደ ርዕሰ ከተማቸው ሲጓዙ እግረ መንገዳቸውን የደብረ ሊባኖስን ገዳም ሊሳለሙ ገብተው ስለነበር አቡነ አብርሃም ‘ሰማይ ሩቅ፤ አደራ ጥብቅ’ ብለው የሰጡኝን አደራ ይረከቡኝ ብለው መጽሐፈ ወንጌሉን ለንጉሠ ነገሥቱ አቀረቡ። ንጉሠ ነገሥቱም መጽሀፉን ወስደው ተጨማሪ ብፅዓት አክለውበት ለገዳሙ መልሰው ሰጥተውታል። ይኼም አዲስ ጽሑፍ፦ “እንደሌለህ የቆጠረህን የሙሶሊኒን ኃይል ከነሠራዊቱ የሰበርክ፤ የተጠቃችውን ኢትዮጵያን በእውነተኛ ፍርድህ የተመካችውን ያላፈርክ፤ ምስጋና ለአንተ ብቻ ይገባል፤ የአገርህን የኢትዮጵያን ነጻነት ለአንተ አደራ እላለሁ፤ እኔ እንደአባቶቼ እንግዳ ነኝ። ነሐሴ ፬ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ቀ.ኃ.ሥ. ንጉሠ ነገሥት” ይላል. የሕንጻው ግንባታ ንጉሠ ነገሥቱ ለገዳሙ ሕንጻ ማሠሪያ መነሻ ይሆን ዘንድ ወጭ አድርገው ለእጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ (በኋላ አቡነ ባስልዮስ) እና ለአባ ሐና ጅማ አስረከቡ። በገንዘቡም አክሲዮን በመግዛትተና በልዩ ልዩ የልማት ሥራ ገቢ እየተደርገ ከ፲፱፻፴፬ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ድረስ ተጠራቅሞ ፩ ሚሊዮን ፪፻፳፮ሺ ፩፻፺፰ ብር ከ፺፩ ሣንቲም ስለደረሰ፤ የቤተ ክርስቲያኑ ሕንፃ ግንባታ የሥራ ጥናት ተጠናቆ ግንቦት ፳፬ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም የመሠረቱ ደንጊያ ተቀመጠ። ለሥራውም ክንውን በልዑል አልጋ ወራሽና በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ የሚመራ ቦርድ ተቋቋመ። የቦርዱም አባላት፦ ልዑል ደጃዝማች አሥራተ ካሣ (በኋላ ልዑል ራሥ) ልዑል ደጃዝማች መንገሻ ሥዩም (በኋላ ልዑል ራሥ) አባ ሐና ጅማ ከ፲፻፶፫ቱ የታኅሣሥ ግርግር በኋላ በሞት የተለዩትን አባ ሐናን በመተካት ብላቴን ጌታ ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል እና ሊቀ-ሥልጣናት ሀብተ ማርያም ወርቅነህ የቦርዱ አባላት ሆነዋል። ይሄ የግንባታ ቦርድ በአጥኚው ኩባንያ እየተረዳ በሥራ ሚኒስቴር መሪነት እየተቆጣጠረ ሥራውን በሚገባ አሠርቶ ካጠናቀቀ በኋላ ግንባታው በተጀመረ በሦስተኛው ዓመት ቅዳሴ ቤቱ ኅዳር ፱ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ተመረቀ። የሕንፃው ፍጆታ (ሀ) ለዋናው ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ሥራ ------------- ፯፻፵፪ ሺ ፫፻፸፭ ብር ከ ፴፫ ሣንቲም (ለ) ለልዩ ልዩ ዕቃና ለሥዕል ሥራ ------------- ፬፻፶፱ ሺ ፯፻፩ ብር ከ ፲፫ ሣንቲም (ሐ)ለአጥር፣ ለድልድልና ለዕቃ ቤት ------------- ፹፰ ሺ ፱፻፲፱ ብር ከ ፹፪ ሣንቲም (መ)ለእንግዶች ማረፊያና ለግቢው አስፋልት ሥራ--------- ፩፻፷፭ ሺ ፬፻፸፱ ብር ከ ፹፯ ሣንቲም (ሠ)ለጥናት መቆጣጠሪያ-------------------- ፩፻፲፮ ሺ ፯፻፱ ብር ከ ፲፭ ሣንቲም (ረ) ለመሐንዲሶች አበልና መጓጓዣ--------------- ፳ ሺ ብር ጠቅላላ ድምር ---------------------------- ፩ ሚሊዮን ፭፻፺፫ ሺ ፩፻፹፭ ብር ከ ፴ ሣንቲም የምረቃው ሥነ ሥርዓት የደብረ ሊባኖስ ገዳም ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ምርቃት ሥነ ሥርዓት ላይ ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር፤ መሳፍንት፤ መኳንንት፤ ሚኒስቴሮችና ሌሎች ባለሥልጣናት ሲገኙ፤ የአዲስ አበባ አድባራት መምህራንና ነዋሪ ሕዝብ ከሰላሌ አውራጃ ሕዝብ ጋር ተሰብስቦ፣ ከዋዜማው ጀምሮ በገዳሙ ክበብ አድሮ ነበር። ሌሊቱን ሁሉ ስብሐተ እግዚአብሔር ሲደርስ አድሮ ከንጋቱ ፲፪ ሰዓት ሲሆን ጸሎተ ቅዳሴው ተጀመረ። የየክፍለ ሀገሩ ሊቃነ ጳጳሳት በ፫ቱ መንበር ተደልድለው ሥርዓተ ቅዳሴውን አካሂደዋል። ከቅዳሴው በኋላ የምረቃው ሥነ ሥርዓት ሲጀመርና የሠሌዳው ጽሑፍ ሲገለጥ፤ ፳፬ ጊዜ መድፍ ተተኮሰ። ንጉሠ ነገሥቱም የሚከተለውን ንግግር አደረጉ። የጻድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ስም በሚጠራበት በዚህ ገዳም የዛሬ ሁለት ዓመት የዚህን ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ የመሠሩትን ድንጋይ ባኖርን ጊዜ እግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ፍጻሜውን እንዲያሳየን ተስፋችንን ገልጠን ነበር። እነሆ ሁሉን ማድረግ የሚቻለውና የለመኑትም የማይነሣ አምላክ የሕንፃውን ሥራ ተፈጽሞ ለማየት አበቃን። ይህን ላደረገልን አምላክ ከምስጋና በቀር ምን ውለታ ልንመልስለት እንችላለን? ኢትዮጵያዊው ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅዱስ ጳውሎስ “ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ ነውን? ወይስ ጭንቀት፤ ወይስ ረኀብ፤ ወይም ራቁትነት ነው?” ብሎ የተናገረውን ቃል ተመልክተው የሐዋርያነት ተግባራቸውን የፈጸሙ፣ ከፍ ያለ ተጋድሎ እና ትሩፋት የሠሩ የክርስትና ዓምድ እንደነበሩ የታመነ ነው። ከሳቸውም ‘የቆብ ልጅ’ ሆነው የታወቁት ገዳማት ብዙ ናቸው። በያለበት ልጆቻቸው ያስተማሩትም ከፍ ያለ ቁጥር ነው። ኢትዮጵያ በአረመኔነትና በእስልምና እንዳትዋጥ አሥግቶ በነበረበት በዚያን ዘመን እርሳቸውና እርሳቸውን የመሳሰሉት ሐዋርያት በሰጡት አገልግሎት ምክንያት ኢትዮጵያ ‘የክርስትና ደሴት’ ተብላ ተጠርታበታለች። ይህን አጋጣሚ ጊዜ ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ ጳጳሳትና የቤተ ክህነት መምህራን የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን አርአያነት በመከተል የክርስትናን ሃይማኖት ለማስፋፋት ድካማቸውን ባለመቆጠብ፣ ራሳቸውን ለዚህ ታላቅ ሐዋርያዊ ተግባር መሥዋዕት በማድረግ እንዲሠሩና እንዲያሠሩ ልናሳስባቸው እንወዳለን። ወንድም ለወንድሙ ከዚህ የበለጠ ትሩፋት ሊሠራለት አይችልም። እኛም በዚህ ገዳም አምላከ ተክለ ሃይማኖት ይህን ቤተ ክርስቲያን በዘመናዊ እቅድ ለማሠራት እንዲያበቃን ብፅዓት አቅርበንለት ነበር። ልመናችንን ሰምቶ ብፅዓታችንን ስለፈጸመልን ለአምላካችን ክብር ምስጋና ይግባው። የሕንፃውን ሥራ እየተቆጣጠረ በሚገባ ለማስፈጸም አደራችንን የጣልንበት በብፁዕ አባታችን አቡነ ባስልዮስ እና በተወደደው ልጃችን በልዑል አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰን ፕሬዚዳንትነት የሚመራው ቦርድ አባሎች ሥራውን በመልካም ስላስፈጸሙ ከልብ እናመሰግናቸዋለን። ወደፊትም ለዚህ ቤተ ክርስቲያን ንጽሕናና መልካም አጠባበቅ አስፈላጊውን ሁሉ እንዲያደርጉ አደራችንን ለፕሬዚዳንቱና ለቦርዱ አባሎች ጥለነዋል። በዚህ ገዳም በጻድቁ ስም ለተሰበሰቡት ምእመናንና አገልጋዮች የግዚአብሔር ረድኤትና የጻድቁ በረከት እንዳይለያቸው እንለምናለን።” በዚህ ዕለት ግምታቸው ሰባ ሺ ብር የሆነ የፋርስ ምንጣፎች በያይነቱ፤ ወርቀ ዘቦ እና ሙካሽ ሥራ ልብሰ ተክህኖ ለ፯ቱ ልዑካን የ ፫ ጊዜ ቅያሪ ሲሰጥ፤ ልዩ ልዩ ንውያተ ቅድስታም እንዲሁ ተሰጥተዋል። በአሁኑ ዘመን በአሁኑ ዘመን፣ ደብረ ሊባኖስ ከ240 በላይ መነኮሳትን ሲያስተናግድ፣ ከዚህ በላይ ብዛት ያላቸውን ምዕመንና ተማላጆችን እንዲሁም ለማኞችን ያስተዳድራል። ገዳሙ በጥንቱ ዘመን ስርዓት መሰረት በመጋቢ የሚመራ ሲሆን ፣ ይህ መጋቢ መነኮሳቱን ለመወከል በተውጣጡ 12 ተወካዮች ላይ ሸንጎ ይይዛል። ዋቢ ምንጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሐዋርያዊ ድርጅት፣ “ትንሣኤ፡ የሃያ አምስት ዓመታት መንፈሳዊ እርምጃ” (፲፱፻፶፱ ዓ/ም) ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት። መደብ :አብያተ ክርስቲያናት መደብ :የኢትዮጵያ ታሪክ
10752
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8B%8D%20%E1%89%A3%E1%8B%B5%E1%88%AD
አው ባድር
ኣው-ባዲር፣ አው-ባድር፣ አባዲር፦ (ዑመር አርሪዳ) (በግምት ወደ ፲፫ ኛው ክ/ዘ)፦ በ ፲፫ ኛው ክ/ዘመን ውስጥ የተፃፈውና ስለ ሐረር ጥንታዊ አፈታሪካዊ ታሪክ የሚዘክረው 'ፋዝ መዲናት ሐረር' የተባለው ያልታተመ መጽሐፍ እንደሚገልጸው አባድር (ዑመር አርሪዳ) እጅግ ከተከበሩት የሐረር ሼኽዎች ውስጥ አንዱና ዋንኛው ናቸው። በዚሁ መጽሓፍ አገላለጽ መሠረት፡ አባድር ከሌሎች በርካታ ሼኾች ጋር በመኾን ከሂጃዝ በ፮፻፩፪ ሂጅሪያ (1216 እ.ኤ.አ) ተነስተው ሐረር ከገቡ በኋላ በአካባቢው የጎሣ እና ኃይማኖት መሪዎች ተመርጠው ዒማም ሆኑ። በቀጣዮቹ ዓመታትም፡ ከተከታዮቻቸው ጋር በመሆን የዚህ ዘመን ፖርቱጋላዊያን ወይም ጣልያኖች ይሆናሉ ተብለው በሚገመቱት የአአዋሚ ንጉሥ ካርቢናል ብ. ማኅራዋል፣ በልጁ ጁርኒያል፣ በሴት ልጁ ማርቃኒሽ(ስ) እና በወንድሙ ሣያደር ላይ በርካታ ጦርነቶችን መርተዋል። እነዚህ ጦርነቶች የተካሄዱት በሐረር ዙርያ ባሉ አካባቢዎች ነው። አባድር በሐረር የአሚሮች ሥም ዝርዝር ውስጥም ሥማቸው ተጠቅሷል። ከዚህ አኳያ ሦስት ዘመናት ከአባድር የግዛት ዘመናት ጋር ተዛምደዋል። እነዚሀም ከ፫፻፩-፬፻፭ ሂጅሪያ (1000-1014 እ.አ.አ)፣ ቀጥሎም ከጥቂት የተቋረጡ የግዛት ዘመናት በኋላ ከ ፬፻፭-፬፻፲፩ ሂጅሪያ፣ እንዲሁም ስማቸው እስከ አኹን ካልታወቁ ገዢዎች የሥልጣን ዘመናት በኋላ ከ፬፻፶፰-፶፱ ሂጅሪያ ባሉት ጊዘያት ውስጥ አባድር አካባቢዉን መርተዋል። አህመድ አስ-ሣሚ የተባለ ጸሓፊ ጃድዋል አስ-ሣስ ወስ-ሣሚ በተባለው መጽሓፉ የአባድርን የግዛት ዘመን ከ ፫፻፴፫-፫፻፶፫ ሂጅሪያ ያደርገዋል። ይህ ስሌት አሳማኝነቱ ያጠራጥራል፤ ምክንያቱም በአው-ባድር የዘር ሐረግ መሠረት፡ ከመጀመሪያው ከሊፋ ኣቡበከር አስ-ስዲቅ (ረዲ አላሁ አንሁ) እስከ አው-ባድር ዘመን ድረስ፡ የሓያ አምስት ትውልድ ልዩነት ሲስላ ፊት ከተጠቀስው ቁጥር ጋር ስለማይሄድ ነው። ከተገለጹት ዘመናት ውስጥ የፋዝ ዘገባ ከአሚሮች ሥም ዝርዝርና የግዛት ዘመናት እና ከአስ-ሣድ የአውባድር ዘመን ቆጠራዎች በተሻለ ከአው-ባድር የዘር ሐረግ ቆጠራ ስሌት ጋር ይቀራረባል። በተለይም በሐረር፡ እስከዚህ ዘመን ድረስ አው-ባድርን የሚያወድሱ፣ የሚዘክሩ በርካታ ዝክሪዎች በየቀኑ ይዘከራሉ። በጥንታዊቷ የሐረር ከተማ ውስጥ፡ የሚገኘውና በአካባቢው ሕዝቦች የሚዘየረው የአው-ባድር የቀብር ሥፍራና ቤት-መስጊድ፡ እንዲሁም ቤት-አሩስ አው-ባድር፦ አው-ባድር የሐረሪ ሤት ያገቡበት ተብሎ የሚታመነው ቤት ሥፍራዎች ለአብነት ይጠቀሳሉ። የአው-ባድር ዝናና መልካም ምግባራት ከሐረር ውጪ ባሉት የኢትዮጵያና አካባቢዋ ባሉ ሙስሊሞች ጭምር በጣም ይከበራሉ፣ ይዘከራሉ። ከአው-ባድር (ዑመር አር-ሪዳ) ሌላ ተመሳሳይ ስም ያላቸው ዑለማዎች በሐረር አቅራቢያ በተለያዩ ዘመናት ኖረዋል። እነኝህም ታላላቅ ዑለማዎች አባድር ሳይህ ዑስማን፣ አባድር ባያዚድ፣ እና ባዴ አባድር ናቸው። 27 መድሃኒያለምና ሙስሊሟ ሀረር እኛ እርስበእርስ ስንናከስ ወይናደጋማዋ ሐረር እርስ በእርሱ ከሚበላላው ጅብ ጋር ሳይቀር ተግባብቶ የሚኖርባት ከተማ ናት፡፡ ሐረር ከአዲስ አበባ ደቡብ ምሥራቅ በአምስት መቶ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተማ ናት። በዘመኑ የአስተዳደር መዋቅር የሃረሪ ክልል ዋና ከተማ ናት። በ1,885 ሜትር ከፍታ ላይ፣ የወይና ደጋ የአይር ጠባይ በተላበሰ ቦታ ላይ አርፋለች። በ1987 ዓመተ ምህረቱ የህዝብ ቆጠራ መሰረት ሐረር 76,378 ሕዝብ ይኖርባታል። ሐረር ለዘመናት ከፍተኛ የንግድ ማዕከል ሆና ስትኖር ከመኻል አገር፣ ከአፍሪካ ቀንድ እና ከአረብ አገራት ጋር በንግድ መንገዶች ስትገናኝ ከቀሪው አለም ጋር ደግሞ በቀይ ባሕር ወደቦች አማካኝነት ትገናኝ ነበር። የሐረር ጀጎል ግንብ ከ1998 ጀምሮ በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ይገኛል። በእስልምና ሃይማኖት "4ኛዋ የተቀደሰች ቦታ" ተብላም ስትታወቅ 82 መስጊዶች፤ አንዳንዶቹ ከ10ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበሩ፤ እንዲሁም 102 የቀብር ቦታዎች አሉዋት ኣው-ባዲር፣ አው-ባድር፣ አባዲር፦ (ዑመር አርሪዳ) (በግምት ወደ ፲፫ ኛው ክ/ዘ)፦ በ ፲፫ ኛው ክ/ዘመን ውስጥ የተፃፈውና ስለ ሐረር ጥንታዊ አፈታሪካዊ ታሪክ የሚዘክረው 'ፋዝ መዲናት ሐረር' የተባለው ያልታተመ መጽሐፍ እንደሚገልጸው አባድር (ዑመር አርሪዳ) እጅግ ከተከበሩት የሐረር ሼኽዎች ውስጥ አንዱና ዋንኛው ናቸው። በዚሁ መጽሓፍ አገላለጽ መሠረት፡ አባድር ከሌሎች በርካታ ሼኾች ጋር በመሆን ከሂጃዝ በ፮፻፩፪ ሂጅሪያ (1216 እ.ኤ.አ) ተነስተው ሐረር ከገቡ በኋላ በአካባቢው የጎሣ እና ኃይማኖት መሪዎች ተመርጠው ዒማም ሆኑ። የሀረር ሕዝብ ታሪክ ፣ ባህል እና ማንነት ከሀረር ከተማ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው፡፡ ሀረሪዎች በረዥም ዘመን የሥልጣኔ ታሪካቸው ያፈሯቸው ተንቀሳቃሽ እና የማይንቀሳቀሱ እንዲሁም የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ በርካታ ቁሳዊ እና መንፈሳዊ ቅርሶች ባለቤት ናቸው፡፡ ከእነዚህ ቅርሶች መካከልም የከተማዋ ልዩ መለያ ምልክት ከመሆንም አልፎ እ.ኤ.አ በ2006 በአለም ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል ግንብ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡በግንቡ ውስጥም ከ82 በላይ መስኪዶች እና በርከት ያሉ የሀረሪ ባህላዊ ቤቶች ይገኛሉ፡፡ ሀረር ከፍተኛ የስልጣኔ እድገት ደረጃ ላይ በደረሰችበት በ16ኛው ክፍለ ዘመንም በምሥራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርት እና የንግድ ማዕከል ሆናም አገልግላለች፡፡ ይህም የበርካታ ታሪካዊ እና ባህላዊ ቅርሶች ባለቤት እንድትሆን አድርጓታል፡፡ የጀጎል ግንብ የሀረሪ ህዝብ የኪነ ህንፃ ችሎታውን የሚያስመሰክር የታሪክ እና የጥበብ መዘክር ነው፡፡ ይህ ግንብ በ16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በአሚር ኑርአማካኝነት እንደተገነባም ይነገራል፡፡ሐረር እንኳን ዛሬ ቀን ዘምኖ ትናንትናም ቢኾን ስንቱ ባሕር አቋርጦ የከተመባት፤ ስንቱ ቅጥሯ ገብቶ ለትውልድ የተረፈ ትዝታ ያስቀመጠባት የውበትና የጥበብ መዲና ናት፡፡ የኢትዮጵያ ኢስላማዊ ኪነ ህንጻና ባህል ማንምም ሳይመስል፤ ሃይማኖታዊ መሰረቱን ሳይጥል የነገሰባት መዲና፤ ያው ጀጉልን መዞር ነው፡፡ በየቦታው መቆም፡፡ በየቦታው ማየት….በየቦታው መደምም…ጀጉልን ገብተው ይኖሯታል እንጂ አይጽፏትም፡፡ ጀጉልን ውስጥ ለውስጥ ከጀመርናት መቆሚያ የለውምና ከጊዜ እየተሻማን በበራፍ በበራፍ እንለፍ ሀረር ከቅርስነት ባሻገር እ.ኤ.አ በ2003/4 በሰላም ፣ በመቻቻል ፣ በመፈቃቀር እና በልማት ከተማነት አለም አቀፍ ሽልማት እና እውቅናን አግኝታለች፡፡ ይህም የተለያየ እምነት ፣ ባህል እና ቋንቋ ያላቸው ህዝቦች ለዘመናት በሰላም እና በፍቅር የኖሩባት እና ዛሬም የሚኖሩባት ከተማ በመሆኗ የተቀዳጀችው ክብር እና እውቅና ነው፡፡ ሀረር ዩኔስኮ ዕውቅናን የቸራት በዓለም ቅርስ ብቻ አይደለም፡፡ ከኪነ ህንጻዎቿ ልቀት ባለፈ ህያው ሆኖ ዛሬም እየኖረ ባለው ሰዋዊ እሴት ምርጥ ነሽ ብሏታል፡፡ ፈረስ መጋላ ይሉታል ሀረሮች ከፊት ለፊቱ የአሚር አብዱላሂ አደራሽ አለ፡፡ ሀረር መድኃኒዓለም በር ላይ፡፡ ጀጉል በሀገራችን በርካታ መስጂዶች የሚገኙባት ከተማ ናት፡፡ በግንብ የተከበበው ቅጥሯ ውስጥ የሚገኘው የመድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ከተማዋ ዩኔስኮ የተባለውን ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ስባ የመቻቻልና የሰላም ተምሳሌት የተባለ እውቅና እንድትቀበል አድርጓታል፡፡ በረዣዥም የመስጂድ ሚናራዎች የታጀበው የሀረር መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን በ27 በድምቀት ይነግሳል፡፡ የጀጉል መንገዶች ከጁምአ ዕለት ድምቀት በተጨማሪ በተለየ 27 ነጠላ ለባሾች ከየአሉበት ወደ ቅጥሯ የሚገቡበት ሌላ ትዕይንት ያስተናግዳሉ፡፡ ምዕተ ዓመት የተሻገረው ይህ ቤተ ክርስቲያን ንጉሰ ነገስቱ አጼ ምኒሊክ ኢትዮጵያን በሚመሩበት ራስ መኮንን የሀረርጌ ገዢ በነበሩበት ዘመን የታነጸ ነው፡፡ ያሰሩት ራስ መኮንን ናቸው፡፡ ክቧ ቤተክርስቲያን ውብ ናት፡፡ ዛፎቿ ጥቂት ናቸው ነገር ግን ከግቢዋ ስፋት አኳያ ጥሩ አድርገው አጅበዋታል፡፡ ዛሬ ከኹሉም አቅጣጫ ሰው ወደ ጀጉል እያመራ ነው፡፡ ሐረር ወይም ዱክ በር ከሚባለው በሗላ በተሽከርካሪ ማለፍ አይቻልም፡፡ ይሄ አጋጣሚ ሌላ ትዕይንት ፈጥሯል፡፡ ነጠላ ያጣፉ ጧፍ የያዙናና ሂጃብ የለበሱ መንገደኞች በጋራ እየተሳሳቁ መንገዱን ሞልተውታል፡፡ እጣንና ጧፍ የዘረጉ ነዋየ ቅድሳት የሚሸጡ መንገዱን ዳርና ዳር ይዘውታል፡፡ የኔ ቢጤዎች ስለ መድሐኒያለም እያሉ ይለምናሉ፡፡ መላው የሐረር ሕዝብ አቦ እንወድኻለን! ሀገርን ለማጥፋት ለመበታተን ቀን ከሌት የሚተጋ መንግስት መሳይ ጊዜ አንግሶት እየገዛን ቢኾንም አንተም እንደኛው በቁምም በስጋም እየሞትክ ቢሆንም አብሽሩ እኛ አንድ ኾነን ሽ የኾንን ኢትዮጵያውያን ነን! የመጣብንን ሰይጣናዊ የጥፋት ውሃ ከአምላክ ጋር አንድ ከኾን እናከሽፈዋለን!!! "ኢትዮጵያ" ማለት መንፈስ ነው፣ እሱም "አንድነት" ማለት ነው፡፡ ኢትዮጵያ የፍቅር ሀገር የመቻቻል ምድር ለዘላለም ትንሩልን!!!! ኢ. ዋግነር፣ ዘ ዲክሽነሪ ኦፍ ኢትዮጵያን ባዮግራፊ፣ ገጽ 1፣ ቮልዩም 1፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናት ኢንስቲትዩት፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ። የኢትዮጵያ ታሪክ የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች
52294
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%A6%E1%88%B5%E1%89%B0%E1%8A%9B%E1%8B%8D%20%E1%89%BB%E1%88%AD%E1%88%88%E1%88%B5
ሦስተኛው ቻርለስ
ቻርለስ፣ የዌልስ ልዑል (ቻርለስ ፊሊፕ አርተር ጆርጅ፣ ህዳር 14 ቀን 1948 ተወለደ) የእንግሊዝ ዙፋን ወራሽ የንግስት ኤልዛቤት የበኩር ልጅ ነው። እ.ኤ.አ. ከ 1952 ጀምሮ የኮርንዋል እና የሮቴሳይ መስፍን ወራሽ ናቸው እና በብሪቲሽ ታሪክ ውስጥ ትልቁ እና ረጅሙ ወራሽ ናቸው ። በተጨማሪም ከጁላይ ወር ጀምሮ የማዕረጉን ማዕረግ የያዙ የዌልስ ልዑል ረጅም ጊዜ የቆዩ ናቸው። 1958. በኤፕሪል 9 ቀን 2021 አባቱ ልዑል ፊሊፕ ሲሞቱ ቻርልስ የኤድንበርግ መስፍንን ማዕረግ ወረሰ። ቻርለስ የንጉሥ ጆርጅ ስድስተኛ እና የንግሥት ኤልዛቤት የመጀመሪያ የልጅ ልጅ ሆኖ በቡኪንግሃም ቤተ መንግሥት ተወለደ። እሱ በ ማጭበርበርእና ጎርደንስቱን ትምህርት ቤቶች የተማረ ሲሆን ሁለቱንም አባቱ በልጅነቱ ይከታተል ነበር። በኋላ በቪክቶሪያ፣ አውስትራሊያ በሚገኘው የጊሎንግ ሰዋሰው ትምህርት ቤት ቲምበርቶፕ ካምፓስ አንድ አመት አሳልፏል። ከካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የአርትስ ባችለር ዲግሪ ካገኘ በኋላ ቻርለስ ከ1971 እስከ 1976 በሮያል አየር ሃይል እና በሮያል ባህር ሃይል አገልግሏል።በ1981 ሌዲ ዲያና ስፔንሰርን አገባ፤ከርሷም ጋር ሁለት ልጆች ዊሊያም እና ሃሪ ወለዱ። እ.ኤ.አ. በ 1996 ጥንዶች በሁለቱም ወገኖች በደንብ የታወቁ ከጋብቻ ውጭ ጉዳዮችን ተከትሎ ተፋቱ። ዲያና በሚቀጥለው ዓመት በፓሪስ የመኪና አደጋ ምክንያት ሞተች። እ.ኤ.አ. በ 2005 ቻርለስ የረጅም ጊዜ አጋር የሆነውን ካሚላ ፓርከር ቦልስን አገባ። የዌልስ ልዑል እንደመሆኑ መጠን ቻርልስ ንግሥቲቱን ወክሎ ኦፊሴላዊ ሥራዎችን ይሠራል። እ.ኤ.አ. በ1976 የፕሪንስ ትረስትን መስርቷል፣ የልዑል በጎ አድራጎት ድርጅቶችን ስፖንሰር ያደርጋል፣ እና ደጋፊ፣ ፕሬዝዳንት ወይም ከ400 በላይ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ድርጅቶች አባል ነው። እንደ የአካባቢ ጥበቃ ተቆርቋሪ ፣ ቻርልስ እንደ ኦርጋኒክ እርሻ እና የአየር ንብረት ለውጥ ባሉ ጉዳዮች ላይ በይፋ ተናግሯል ፣ ይህም ከአካባቢ ጥበቃ ቡድኖች ሽልማት እና እውቅና አግኝቷል ። ሆሚዮፓቲ (ሆሚዮፓቲ)ን ጨምሮ ለአማራጭ ሕክምና የሚሰጠው ድጋፍ የትችት ርዕሰ ጉዳይ ሆኗል። በህብረተሰቡ ውስጥ ስላለው የስነ-ህንፃ ሚና እና ስለ ታሪካዊ ሕንፃዎች ጥበቃ ያለው አመለካከት ከብሪቲሽ አርክቴክቶች እና ዲዛይን ተቺዎች ከፍተኛ ትኩረት አግኝቷል። ከ 1993 ጀምሮ ቻርለስ በሥነ ሕንፃ ጣዕሙ ላይ የተመሠረተ የሙከራ አዲስ ከተማ የሆነውን ፓውንድበሪ በመፍጠር ላይ ሰርቷል። እሱ ደግሞ የበርካታ መጽሃፎች ደራሲ ወይም ተባባሪ ደራሲ ነው። የመጀመሪያ ህይወት, ቤተሰብ እና ትምህርት ቻርልስ የተወለደው በቡኪንግሃም ቤተመንግስት እ.ኤ.አ. ህዳር 14 ቀን 1948 በእናቱ አያቱ ጆርጅ ስድስተኛ የግዛት ዘመን ፣ የልዕልት ኤልሳቤጥ ፣ የኤድንበርግ ዱቼዝ እና የፊሊፕ ፣ የኤድንበርግ መስፍን የመጀመሪያ ልጅ ሆኖ ነበር ። እ.ኤ.አ. በታህሳስ 15 ቀን 1948 የካንተርበሪው ሊቀ ጳጳስ ጆፍሪ ፊሸር ተጠመቁ ። የአያቱ ሞት እና እናቱ በ 1952 ንግሥት ኤልዛቤት ሆነው መገኘታቸው ቻርለስን አልጋ ወራሽ አድርጎታል። የንጉሠ ነገሥቱ የበኩር ልጅ እንደመሆኖ፣ የኮርንዋል መስፍን፣ የሮተሳይ መስፍን፣ የካሪክ አርል፣ የሬንፍሬው ባሮን፣ የደሴቶች ጌታ፣ እና የስኮትላንድ ልዑል እና ታላቁ መጋቢ የሚሉ ርዕሶችን ወዲያውኑ ወሰደ። ሰኔ 2 ቀን 1953 ቻርለስ የእናቱ ዘውድ በዌስትሚኒስተር አቤይ ተገኝቷል። በጊዜው የከፍተኛ ክፍል ልጆች እንደተለመደው ካትሪን ፒብልስ የተባለች አስተዳዳሪ ተሹሞ ትምህርቱን የጀመረው ከአምስት እስከ ስምንት ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ ነበር። ቡኪንግሃም ቤተ መንግስት እ.ኤ.አ. በ1955 ቻርልስ የግል ሞግዚት ከመያዝ ይልቅ ትምህርት ቤት እንደሚማር አስታውቆ ነበር፣ በዚህም መንገድ የተማረ የመጀመሪያ ወራሽ አድርጎታል። እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 7 1956 ቻርልስ በምዕራብ ለንደን በሚገኘው የሂል ሃውስ ትምህርት ቤት ትምህርቶችን ጀመረ። ከትምህርት ቤቱ መስራች እና ርእሰመምህር ስቱዋርት ታውንንድ የተለየ እንክብካቤ አላገኘም ፣ ንግስቲቱ ቻርለስ በእግር ኳስ እንዲሰለጥናት ምክሯን አቅርቧል ምክንያቱም ልጆቹ በእግር ኳስ ሜዳ ውስጥ ለማንም የማይታዘዙ ናቸው። ከዚያም ቻርለስ ከ1958 ጀምሮ በስኮትላንድ ሰሜናዊ ምስራቅ ጎርደንስቶውን ተከትሎ በበርክሻየር፣ እንግሊዝ በሚገኘው የ መሰናዶ ትምህርት ቤት ሁለቱን የአባቱን የቀድሞ ትምህርት ቤቶች በኤፕሪል 1962 ትምህርት ጀመረ።በተለይ በጠንካራ ሥርዓተ ትምህርቱ የሚታወቀውን ጎርዶንስቶንን “” ሲል እንደገለጸው፣ ቻርልስ በመቀጠል ጎርዶንስቶንን “ስለ ራሴ እና ስለራሴ ችሎታዎች እና እጥረቶች ብዙ እንዳስተማረው በመግለጽ ተግዳሮቶችን እንድቀበል አስተምሮኛል። ቅድሚያውን ይውሰዱ። እ.ኤ.አ. በ 1975 በሰጠው ቃለ መጠይቅ ፣ ጎርደንስቶውን በመሳተፉ “ደስተኛ” እንደሆነ እና “የቦታው ጥንካሬ” “በጣም የተጋነነ ነው” ብሏል። እ.ኤ.አ. በ1966 በቪክቶሪያ ፣ አውስትራሊያ በሚገኘው የጊሎንግ ሰዋሰው ትምህርት ቤት ቲምበርቶፕ ካምፓስ ሁለት ጊዜ አሳልፈዋል ፣ በዚህ ጊዜ ከታሪክ አስተማሪው ሚካኤል ኮሊንስ ፐርሴ ጋር ለትምህርት ፓፑዋ ኒው ጊኒ ጎብኝተዋል። እ.ኤ.አ. በ 1973 ቻርልስ በቲምበርቶፕ ያሳለፈውን ጊዜ የሙሉ ትምህርቱ በጣም አስደሳች ክፍል አድርጎ ገልጿል። ወደ ጎርዶንስቶውን ሲመለስ ቻርልስ አባቱን በመምሰል ሄድ ልጅ ለመሆን ቻለ። በ1967 ስድስት -ደረጃዎችን እና ሁለት -ደረጃዎችን በታሪክ እና በፈረንሳይኛ በቅደም ተከተል እና ክፍሎች ለቅቋል። በቅድመ ትምህርቱ፣ ቻርልስ በኋላ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡- “ትምህርት የሚኖረኝን ያህል አልተደሰትኩም፣ ግን ይህ የሆነው ከየትኛውም ቦታ ይልቅ ቤት ውስጥ ደስተኛ ስለሆንኩ ብቻ ነው። ቻርልስ የብሪቲሽ ጦር ኃይሎችን ከመቀላቀል ይልቅ ከኤ-ደረጃው በኋላ በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲሄድ ንጉሣዊውን ባህል ለሁለተኛ ጊዜ ሰበረ። በጥቅምት 1967 በካምብሪጅ ትሪኒቲ ኮሌጅ ገብተው የአርኪኦሎጂ እና አንትሮፖሎጂን ለመጀመሪያ ጊዜ የትሪፖስ ክፍል አንብበው ለሁለተኛው ክፍል ወደ ታሪክ ተቀይረዋል ። በሁለተኛው አመቱ፣ ቻርልስ የዌልስን ታሪክ እና ቋንቋ ለተወሰነ ጊዜ በማጥናት በአበርስትዊዝ የዌልስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ገብቷል። ከካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ በ2፡2 ባችለር ኦፍ አርት (ቢኤ) ዲግሪ በጁን 23 ቀን 1970 ተመረቀ፣ የዩኒቨርሲቲ ዲግሪ ያገኘ የመጀመሪያው የእንግሊዝ አልጋ ወራሽ። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 2 ቀን 1975 በካምብሪጅ የኪነጥበብ ማስተር (ኤምኤ ካንታብ) ዲግሪ ተሰጠው። በካምብሪጅ፣ አርትስ ማስተር የአካዳሚክ ደረጃ እንጂ የድህረ ምረቃ ዲግሪ አይደለም። የዌልስ ልዑል የዌልስ ልዑል ቻርለስ የዌልስ ልዑል እና የቼስተር አርል በጁላይ 26 ቀን 1958 ተፈጠረ ፣ ምንም እንኳን ኢንቬስትመንት እስከ ጁላይ 1 1969 ባይቆይም ፣ በእናቱ በኬርናርፎን ቤተመንግስት በተካሄደ የቴሌቪዥን ሥነ ሥርዓት ላይ ዘውድ ሲቀዳጅ ። እ.ኤ.አ. በ1976 በመመስረት እና በ1981 ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ተጉዘዋል።በ1970ዎቹ አጋማሽ ላይ ልዑሉ የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ማልኮም ባቀረቡት ሀሳብ የአውስትራሊያ ጄኔራል ገዥ ሆነው የማገልገል ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀው ተጨማሪ ህዝባዊ ተግባራትን ይፈፅማሉ። ፍሬዘር፣ ነገር ግን በህዝባዊ ጉጉት እጦት ምክንያት ከፕሮፖዛሉ ምንም አልመጣም። ቻርለስ አስተያየት ሰጥቷል፡ "ታዲያ አንድ ነገር ለመርዳት ስትዘጋጅ እና እንደማትፈልግ ሲነገርህ ምን ማሰብ አለብህ?" ቻርለስ በኤድዋርድ ሰባተኛ በሴፕቴምበር 9 2017 ተይዞ የነበረውን ሪከርድ በማለፍ የዌልስ ረጅሙ ልዑል ነው።እርሱ አንጋፋ እና ረጅም ጊዜ ያገለገሉ የብሪታኒያ አልጋ ወራሽ፣ የኮርንዎል የረዥም ጊዜ መስፍን እና የረጅም ጊዜ የስልጣን ዘመን መስፍን ናቸው። ንጉሠ ነገሥት ከሆነ በ 1830 ሲነግሥ 64 ዓመቱ የነበረው ዊልያም አራተኛ ፣ የወቅቱ ትልቁ ሰው ይሆናል ። ኦፊሴላዊ ግዴታዎች እ.ኤ.አ. በ 2008 ዘ ዴይሊ ቴሌግራፍ ቻርልን “የንጉሣዊው ቤተሰብ በጣም ታታሪ አባል” ሲል ገልጾታል። በ2008 560 ይፋዊ ተሳትፎዎችን፣ በ2010 499 እና በ2011 ከ600 በላይ ስራዎችን ሰርቷል። የዌልስ ልዑል በጁላይ 1970 በዩናይትድ ስቴትስ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ በኦቫል ኦፊስ ውስጥ ከዩኤስ ፕሬዝዳንት ሪቻርድ ኒክሰን ጋር ተገናኘ። የዌልስ ልዑል እንደመሆኑ መጠን ቻርልስ ንግሥቲቱን ወክሎ ኦፊሴላዊ ሥራዎችን ይሠራል። እሱ ኢንቨስትመንቶችን ያስተዳድራል እና የውጭ አገር መሪዎችን የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ይሳተፋል። ልዑል ቻርለስ በየክረምት የአንድ ሳምንት ተሳትፎን በመፈጸም እና እንደ ሴኔድ መክፈቻ ባሉ አስፈላጊ ሀገራዊ ዝግጅቶች ላይ በመገኘት የዌልስ መደበኛ ጉብኝቶችን ያደርጋል። የሮያል ስብስብ ትረስት ስድስቱ ባለአደራዎች በዓመት ሦስት ጊዜ በሊቀመንበርነት ይገናኛሉ። ልዑል ቻርለስ ዩናይትድ ኪንግደምን ወክሎ ወደ ውጭ አገር ተጓዘ። ቻርለስ እንደ ሀገር ውጤታማ ተሟጋች ተደርጎ ተቆጥሯል። እ.ኤ.አ. በ1983 በንግሥቲቱ ላይ በ.22 ጠመንጃ የተኮሰው ክሪስቶፈር ጆን ሌዊስ ከዲያና እና ዊሊያም ጋር ኒውዚላንድን እየጎበኘ ያለውን ቻርለስን ለመግደል ከአእምሮ ህክምና ሆስፒታል ለማምለጥ ሞከረ። እ.ኤ.አ. ጥር 1994 አውስትራሊያን እየጎበኘ ሳለ በአውስትራሊያ ቀን በዴቪድ ካንግ በርካታ መቶ የካምቦዲያ ጥገኝነት ጠያቂዎችን በማቆያ ካምፖች ውስጥ ያለውን አያያዝ በመቃወም ከመነሻ ሽጉጥ ሁለት ጥይቶች ተኮሱበት። በ1995 ቻርልስ የንጉሣዊው የመጀመሪያው አባል ሆነ። ቤተሰብ በይፋዊ አቅም የአየርላንድ ሪፐብሊክን ለመጎብኘት. እ.ኤ.አ. በ 2000 ፣ ቻርለስ የዌልስ ብሔራዊ መሣሪያ የሆነውን በገና በመጫወት የዌልስ ተሰጥኦ ለማዳበር የዌልስ ልዑል ኦፊሴላዊ የበገና ዘበኛ የማድረግ ባህልን አነቃቃ። እሱ እና የኮርንዋል ዱቼዝ የበርካታ የስኮትላንድ ድርጅቶች ጠባቂ በሆነበት በስኮትላንድ ውስጥ በየዓመቱ አንድ ሳምንት ያሳልፋሉ። ለካናዳ ጦር ሃይል ያለው አገልግሎት ስለ ሰራዊት እንቅስቃሴ እንዲያውቀው ያስችለዋል፣ እና በካናዳ ወይም በባህር ማዶ እያለ እነዚህን ወታደሮች እንዲጎበኝ እና በክብረ በዓሉ ላይ እንዲሳተፍ ያስችለዋል። ለምሳሌ እ.ኤ.አ. በ2001 ከፈረንሳይ ጦር ሜዳዎች በተወሰዱ እፅዋት የተሰራ ልዩ ልዩ የሆነ የአበባ ጉንጉን በካናዳ የማይታወቅ ወታደር መቃብር ላይ አስቀመጠ እና በ1981 የካናዳ የጦር አውሮፕላን ቅርስ ሙዚየም ጠባቂ ሆነ። እ.ኤ.አ. በ 2005 በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጆን ፖል የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ቻርልስ ሳይታሰብ ውዝግብ አስነስቷል ፣ ከጎናቸው ከተቀመጡት የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ጋር ሲጨባበጥ ። የቻርለስ ፅህፈት ቤት በመቀጠል መግለጫውን አውጥቷል፡- “የዌልስ ልዑል በመገረም ተይዟል እናም የሚስተር ሙጋቤን እጅ ከመጨባበጥ ለመቆጠብ አልቻለም። ልዑሉ አሁን ያለውን የዚምባብዌ አገዛዝ አስጸያፊ ሆኖ አግኝተውታል። የሚሠራውን የዚምባብዌ መከላከያ እና የእርዳታ ፈንድ ደግፈዋል። በህዳር 2001 ቻርለስ በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ ከሚገኙት አሊና ሌቤዴቫ በቀይ ሥጋ ሥጋ ተመታ። በላትቪያ ይፋዊ ጉብኝት ላይ ነበር።እ.ኤ.አ. በ 2010 ቻርልስ ንግሥቲቱን ወክለው በ 2010 የኮመንዌልዝ ጨዋታዎች የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ በዴሊ ፣ ሕንድ ውስጥ። በዩናይትድ ኪንግደም የኮመንዌልዝ ሀገራትን ለመደገፍ እንደ እ.ኤ.አ. በ 2011 በዌስትሚኒስተር አቢ የተካሄደው የክሪስቸርች የመሬት መንቀጥቀጥ መታሰቢያ አገልግሎት በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ይሳተፋል ። ከህዳር 15 እስከ 17 ቀን 2013 ንግስቲቱን ለመጀመሪያ ጊዜ በኮመንዌልዝ የመሪዎች ስብሰባ ላይ ወክሏል ። በኮሎምቦ፣ ስሪላንካ እ.ኤ.አ. በ 2004 እና በ 2005 ልዑል ቻርልስ ለመንግስት ሚኒስትሮች የላካቸው ደብዳቤዎች - ጥቁር የሸረሪት ማስታወሻዎች የሚባሉት - በ 2000 የመረጃ ነፃነት ህግ ስር ደብዳቤዎቹን ለመልቀቅ ዘ ጋርዲያን ጋዜጣ ፈታኝ ሁኔታን ተከትሎ ሊያሳፍር ይችላል ። በመጋቢት 2015 ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዩናይትድ ኪንግደም የልዑል ደብዳቤዎች እንዲለቀቁ ወሰነ. ደብዳቤዎቹ የታተሙት በካቢኔ ጽሕፈት ቤት እ.ኤ.አ. ማስታወሻዎቹ በጋዜጣው ላይ “አስደሳች” እና “ጉዳት የለሽ” በሚል በተለያየ መንገድ የተገለጹ ሲሆን መፈታታቸውም “እሱን ለማሳነስ በሚጥሩት ላይ የተቃረበ ነው” ሲሉ በህዝቡም ምላሽ ሰጥተዋል። በግንቦት 2015 የዌልስ ልዑል እና የኮርንዋል ዱቼዝ የመጀመሪያ የጋራ ጉብኝታቸውን ወደ አየርላንድ ሪፐብሊክ አደረጉ።ጉዞው በብሪቲሽ ኤምባሲ “ሰላምና እርቅን ለማስፈን” ጠቃሚ እርምጃ ተብሎ ተጠርቷል። በጉዞው ወቅት ቻርለስ ከሲን ፊን እና ከአይአርኤ መሪ ከሚባሉት ጄሪ አዳምስ ጋር በጋልዌይ ተጨባበጡ።ይህም በመገናኛ ብዙሃን “ታሪካዊ መጨባበጥ” እና “ለአንግሎ-አይሪሽ ግንኙነት ትልቅ ቦታ የሚሰጠው” ሲል ገልጿል። የልዑሉን ጉብኝት ለማድረግ በተቃረበበት ወቅት፣ ሁለት የአየርላንድ ሪፐብሊካን ተቃዋሚዎች የቦምብ ጥቃት በማቀድ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ሴምቴክስ እና ሮኬቶች በደብሊን የተጠረጠሩት ዶናል ኦ ኮይስዴልብሃ ፣የራስ የሚል ስም ያለው ድርጅት አባል ሲሆን በኋላም ለአምስት ዓመት ተኩል ታስሯል። ለ 11 ዓመት ተኩል ታስሮ ከነበረው የሪል አባል የሆነው የካውንቲ ሉዝ ሲሙስ ማክግሬን ከአርበኞች ሪፐብሊካን ጋር ተገናኝቷል። በ2015 ልዑል ቻርልስ ሚስጥራዊ የእንግሊዝ ካቢኔ ወረቀቶችን ማግኘት እንደቻለ ተገለጸ። ቻርለስ ከንግሥቲቱ፣ ቴሬዛ ሜይ፣ ዶናልድ ትራምፕ እና ሌሎች የዓለም መሪዎች ጋር የዲ-ዴይ 75ኛ ዓመትን በጁን 5 2019 ለማክበር እንደ ሲስተምስ ላሉት ኩባንያዎች የጦር መሳሪያ ወደ ውጭ መላክን ለማስተዋወቅ ቻርለስ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ተደጋጋሚ ጉብኝት አድርጓል። እ.ኤ.አ. በ 2013 ፣ 2014 እና 2015 ከሳውዲ አረቢያ ብሄራዊ ጥበቃ አዛዥ ሙተይብ ቢን አብዱላህ ጋር ተገናኝተዋል። እ.ኤ.አ. በዚሁ ፌስቲቫል ላይ የብሪታኒያ የጦር መሳሪያ ኩባንያ ሲስተምስ በልዑል ሳልማን ቢን አብዱላዚዝ ተሸልሟል። ቻርለስ በ2016 በስኮትላንዳዊው የፓርላማ አባል ማርጋሬት ፌሪየር ቲፎን ተዋጊ ጄቶች ለሳውዲ አረቢያ በመሸጥ ላይ በነበራቸው ሚና ተነቅፈዋል። የቻርለስ የህይወት ታሪክ ተመራማሪ ካትሪን ማየር የታይም መጽሄት ጋዜጠኛ ከልዑል ቻርለስ የውስጥ ክበብ ውስጥ በርካታ ምንጮችን ቃለ መጠይቅ እንዳደረገ የሚናገረው እንደገለጸው ከሳውዲ አረቢያ እና ከሌሎች የአረብ ባህረ ሰላጤ ሀገራት ጋር በሚደረግ ስምምነት "መሳሪያ ለገበያ መጠቀምን አይወድም"። እንደ ሜየር ገለጻ፣ ቻርለስ ተቃውሞውን ያነሳው በውጭ አገር የጦር መሣሪያዎችን በግል ለመሸጥ ብቻ ነው። የኮመንዌልዝ መንግስታት መሪዎች በ 2018 ባደረጉት ስብሰባ የዌልስ ልዑል ከንግስቲቱ በኋላ ቀጣዩ የኮመንዌልዝ ርዕሰ ጉዳይ እንደሚሆን ወስነዋል ። ጭንቅላቱ ተመርጧል ስለዚህም በዘር የሚተላለፍ አይደለም. እ.ኤ.አ. ማርች 7 2019 ንግስት የዌልስ ልዑል የቻርልስ ኢንቬስትመንት የተደረገበትን 50ኛ ዓመት ለማክበር የቡኪንግ ቤተመንግስት ዝግጅት አስተናግዳለች። በክስተቱ ላይ እንግዶች የኮርንዋል ዱቼዝ፣ የካምብሪጅ ዱክ እና ዱቼዝ፣ የሱሴክስ ዱክ እና ዱቼዝ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ እና የዌልስ የመጀመሪያ ሚኒስትር ማርክ ድራክፎርድ ይገኙበታል። በዚያው ወር የእንግሊዝ መንግስት ባቀረበው ጥያቄ የዌልስ ልዑል እና የኮርንዋል ዱቼዝ ወደ ኩባ ይፋዊ ጉብኝት በማድረግ ሀገሩን የጎበኙ የመጀመሪያ የእንግሊዝ ንጉሣዊ ቤተሰብ አደረጓቸው። ጉብኝቱ በዩኬ እና በኩባ መካከል የቅርብ ግንኙነት ለመፍጠር ጥረት ተደርጎ ታይቷል። እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 2021 ቻርለስ ባርባዶስ ወደ ፓርላሜንታዊ ሪፐብሊክ መሸጋገሯን ለማክበር በተደረጉ ስነ ስርዓቶች ላይ ተገኝቷል፣ በ25 ማርች 2020፣ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ቻርልስ ኮቪድ-19 እንደያዘ ተገለጸ። እሱ እና ሚስቱ በመቀጠል በበርክሃል መኖሪያቸው ተገለሉ። ካሚላ እንዲሁ ተፈትኗል ፣ ግን አሉታዊ ውጤት ተመለሰ። ክላረንስ ሃውስ "ቀላል ምልክቶች" እንዳሳዩ ነገር ግን "በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚቆይ" ተናግሯል. በተጨማሪም “ልዑሉ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ባደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ የተነሳ ቫይረሱን ከማን እንደያዘ ማረጋገጥ አይቻልም” ብለዋል ። ብዙ ጋዜጦች ቻርልስ እና ካሚላ ብዙ የኤንኤችኤስ ዶክተሮች፣ ነርሶች እና ታካሚዎች በፍጥነት መሞከር ባልቻሉበት ጊዜ ወዲያውኑ እንደተፈተኑ ወሳኝ ነበሩ። እ.ኤ.አ. ማርች 30 ቀን 2020 ክላረንስ ሀውስ ቻርልስ ከቫይረሱ ማገገሙን እና ሐኪሙን ካማከሩ በኋላ ማግለሉን አቁሟል። ከሁለት ቀናት በኋላ ማህበራዊ ርቀትን መለማመዱን እንደሚቀጥል በቪዲዮ ገልጿል። እ.ኤ.አ. በየካቲት 2021 ቻርልስ እና ባለቤቱ የኮቪድ-19 ክትባት መጠን አግኝተዋል። ወታደራዊ ሙያ ዘመን ቻርለስ በሮያል አየር ኃይል ውስጥ አገልግሏል እና የአባቱን፣ የአያቱን እና የሁለቱን ቅድመ አያቶቹን ፈለግ በመከተል በሮያል ባህር ኃይል ውስጥ አገልግሏል። በካምብሪጅ በሁለተኛው አመት የሮያል አየር ሃይል ስልጠና ጠየቀ እና ተቀበለ። እ.ኤ.አ. ማርች 8 ቀን 1971 እንደ ጄት አብራሪ ለማሰልጠን እራሱን ወደ ሮያል አየር ኃይል ኮሌጅ ክራዌል በረረ። በሴፕቴምበር ካለፈዉ ሰልፍ በኋላ በባህር ኃይል ስራ ጀመረ እና በሮያል ባህር ሃይል ኮሌጅ ዳርትማውዝ የስድስት ሳምንት ኮርስ ገባ። ከዚያም በተመራው ሚሳኤል አጥፊ ኤችኤምኤስ ኖርፎልክ እና ፍሪጌቶቹ ኤችኤምኤስ ሚነርቫ እና ኤችኤምኤስ ጁፒተር አገልግለዋል። እ.ኤ.አ. በ 1974 ፣ በ ሄሊኮፕተር አብራሪ ለመሆን ብቁ ሆነ ፣ እና ከ 845 የባህር ኃይል አየር ጓድሮን ጋር ተቀላቅሏል ፣ ከኤችኤምኤስ ሄርሜስ ። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በቺፕመንክ መሰረታዊ አብራሪ አሰልጣኝ፣ በ ጄት ፕሮቮስት ጄት አሰልጣኝ እና በቢግል ባሴት ባለብዙ ሞተር አሰልጣኝ ላይ መብረርን ተማረ። እ.ኤ.አ. በ 1994 በሄብሪድስ ውስጥ 146 ን ከአደጋ በኋላ በረራውን እስኪያቋርጥ ድረስ ሃውከር ሲዴሊ አንዶቨር ፣ ዌስትላንድ ዌሴክስ እና ቢኤ 146 አውሮፕላኖች በመደበኛነት ይበር ነበር ። ግንኙነቶች እና ትዳሮች የመጀመሪያ ዲግሪ በወጣትነቱ፣ ቻርለስ ከበርካታ ሴቶች ጋር በፍቅር ተቆራኝቷል። ታላቅ አጎቱ ሎርድ ማውንባተን እንዲህ ብሎ መከረው፡- እንዳንተ አይነት ሰውዬው ከመረጋጋቱ በፊት የቻለውን ያህል የጫካ አጃውን ዘርቶ ብዙ ጉዳዮችን ማድረግ ይኖርበታል፤ ለሚስት ግን ተስማሚ፣ ማራኪ እና ጣፋጭ ባህሪ ያለው ልጅ ይመርጥ ከማንም ጋር ሳታገኛት በፊት። በፍቅር መውደቅህ ... ሴቶች ከጋብቻ በኋላ በእግራቸው ላይ መቆየት ካለባቸው ልምድ ማግኘታቸው ይረብሻል። የቻርልስ የሴት ጓደኞች በስፔን የብሪታንያ አምባሳደር የነበሩትን የሰር ጆን ራሰል ሴት ልጅ ጆርጂያና ራሰልን ያካትታሉ። የዌሊንግተን 8ኛ መስፍን ሴት ልጅ ሌዲ ጄን ዌልስሊ; ዴቪና ሼፊልድ; እመቤት ሳራ ስፔንሰር; እና ካሚላ ሻንድ በኋላ ሁለተኛ ሚስቱ እና የኮርንዋል ዱቼዝ ሆነች። እ.ኤ.አ. በ 1974 መጀመሪያ ላይ ፣ የሞንባንተን የልጅ ልጅ ከሆነችው አማንዳ ክናችቡል ጋር ሊኖር ስለሚችለው ጋብቻ ከቻርልስ ጋር መፃፍ ጀመረ። ቻርልስ ለአማንዳ እናት - እመቤት ብራቦርን ሴት ልጇን እንደምትፈልግ በመግለጽ ደብዳቤ ጽፋለች ፣ ምንም እንኳን ገና የ17 ዓመቷ ልጃገረድ ጋር መጠናናት ያለጊዜው እንደሆነ ጠቁማለች ። ከአራት አመታት በኋላ, የሞንባንተንበ 1980 የህንድ ጉብኝት ላይ አማንዳ እና እራሱ ከቻርለስ ጋር እንዲሄዱ አመቻችቷል. ሁለቱም አባቶች ግን ተቃውመዋል; ፊሊፕ ቻርለስ በታዋቂው አጎቱ (የመጨረሻው የብሪቲሽ ምክትል እና የህንድ የመጀመሪያ ጠቅላይ ገዥ ሆነው ያገለገሉት) ይገለበጣሉ ብሎ ፈርቶ ነበር፣ ሎርድ ብራቦርን ግን የጋራ ጉብኝት የአጎት ልጆች ለመሆን ከመወሰናቸው በፊት የመገናኛ ብዙሃን ትኩረት እንደሚያደርግ አስጠንቅቋል። ጥ ን ድ. ሆኖም፣ በነሐሴ 1979፣ ቻርለስ ብቻውን ወደ ሕንድ ከመሄዱ በፊት፣ የሞንባንተን በ ተገደለ። ቻርለስ ሲመለስ ለአማንዳ ጥያቄ አቀረበ፣ ነገር ግን ከአያቷ በተጨማሪ፣ በቦምብ ጥቃቱ የአባት ቅድመ አያቷን እና ታናሽ ወንድሟን ኒኮላስን አጥታለች እና አሁን ወደ ንጉሣዊ ቤተሰብ ለመግባት ፈቃደኛ አልነበረችም። በሰኔ 1980 ቻርልስ ቼቨኒንግ ሀውስን በይፋ ውድቅ አደረገች። ከ 1974 ጀምሮ እንደ የወደፊት መኖሪያው በእጁ ላይ ተቀምጧል. ቼቨኒንግ ፣ በኬንት ውስጥ የሚያምር ቤት ፣ ቻርልስ በመጨረሻ እንደሚይዘው በማሰብ በመጨረሻው ኤርል ስታንሆፕ ፣ አማንዳ ልጅ የለሽ ታላቅ አጎት ከስጦታ ጋር ዘውዱ ተረክቧል። እ.ኤ.አ. በ 1977 የጋዜጣ ዘገባ ከሉክሰምበርግ ልዕልት ማሪ-አስትሮድ ጋር መገናኘቱን በስህተት አሳወቀ ። ከሴት ዲያና ስፔንሰር ጋር ጋብቻ ዋና መጣጥፍ፡ የልዑል ቻርልስ እና እመቤት ዲያና ስፔንሰር ሰርግ የዌልስ ልዑል እና ልዕልት በአውስትራሊያ ውስጥ ን ጎበኙ፣ መጋቢት 1983 ቻርለስ መጀመሪያ የተገናኘው ሌዲ ዲያና ስፔንሰርን በ 1977 ቤቷን አልቶርፕ ሲጎበኝ ነበር። እሱ የታላቅ እህቷ የሳራ ጓደኛ ነበር፣ እና እስከ 1980 አጋማሽ ድረስ ዲያናን በፍቅር አላገናዘበም። በጁላይ ወር ቻርልስ እና ዲያና በአንድ የጓደኛቸው ባርቤኪው ላይ በሳር ጭድ ላይ አንድ ላይ ተቀምጠው ሳለ፣ በአያቱ ጌታ ተራራባተን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ትጉ እና እንክብካቤ እንደሚያስፈልገው ገልጻለች። ብዙም ሳይቆይ የቻርልስ የተመረጠ የህይወት ታሪክ ጸሐፊ ጆናታን ዲምብልቢ እንዳለው “ምንም ዓይነት ስሜት ሳይታይበት፣ እሷን እንደ ሙሽሪት በቁም ነገር ያስብላት ጀመር”፣ እና እሷ ቻርለስን ወደ ባልሞራል ካስትል እና ሳንድሪንግሃም ሃውስ በመጎብኘት አብራው ነበር። የቻርለስ የአጎት ልጅ ኖርተን ክናችቡል እና ባለቤቱ ለቻርልስ ዲያና በአቋሙ የተደናገጠች መስሎ እንደታየች እና ከእርሷ ጋር ፍቅር ያለው አይመስልም። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የጥንዶቹ ቀጣይ የፍቅር ጓደኝነት የፕሬስ እና የፓፓራዚን ትኩረት ስቧል። ልዑል ፊልጶስ ቻርልስ በቅርቡ እሷን ለማግባት ውሳኔ ላይ ካልደረሰ እና እሷም ተስማሚ ንጉሣዊ ሙሽራ መሆኗን (በተራራባተንመስፈርት) ከተገነዘበ የመገናኛ ብዙኃን ግምቶች የዲያናን ስም እንደሚጎዱ ሲነግሩት ቻርልስ የአባቱን ምክር እንደ ማስጠንቀቂያ ወስዶታል። ያለ ተጨማሪ መዘግየት ለመቀጠል. ልዑል ቻርለስ በየካቲት 1981 ለዲያና አቀረበ ። ተቀብላ በቅዱስ ጳውሎስ ካቴድራል ሐምሌ 29 ቀን ተጋቡ። በጋብቻው ወቅት፣ ቻርለስ የበጎ ፈቃድ ታክስ መዋጮውን ከ 50 በመቶው ወደ 25 በመቶ ዝቅ ብሏል ዱቺ ኦፍ ኮርንዋል ትርፍ። ጥንዶቹ በኬንሲንግተን ቤተ መንግሥት እና በቴትበሪ አቅራቢያ በሚገኘው ሃይግሮቭ ሃውስ ውስጥ ይኖሩ ነበር፣ እና ሁለት ልጆችን ወልደው ነበር፡- ፕሪንስ ዊሊያም (እ.ኤ.አ. 1982) እና ሄንሪ ("ሃሪ" በመባል የሚታወቁት) (ቢ. 1984)። ቻርልስ በልጆቹ ልደት ወቅት የመጀመሪያው የንጉሣዊ አባት በመሆን ምሳሌን አስቀምጧል። በአምስት አመት ውስጥ ጋብቻው በጥንዶች አለመጣጣም እና በ13 አመት እድሜ ልዩነት ምክንያት ችግር ተፈጠረ። በ1992 ፒተር ሴተለን በቀረፀው የቪዲዮ ቀረጻ ላይ ዲያና በ1986 “በዚህ አካባቢ ከሚሰራ ሰው ጋር ጥልቅ ፍቅር እንደነበረው” ተናግራለች። እ.ኤ.አ. በ 1986 ወደ ዲፕሎማቲክ ጥበቃ ቡድን የተዛወረውን ባሪ ማንናኪን እየተናገረች ነው ተብሎ የሚታሰበው ሥራ አስኪያጆቹ ከዲያና ጋር ያለው ግንኙነት አግባብ አለመሆኑን ካረጋገጡ በኋላ ነው። ዲያና ከጊዜ በኋላ የቤተሰቡ የቀድሞ የማሽከርከር አስተማሪ ከሆነው ከሜጀር ጄምስ ሂዊት ጋር ግንኙነት ጀመረች። የቻርለስ እና የዲያና አለመመቸት አንዳቸው በሌላው ኩባንያ ውስጥ በፕሬስ "" የሚል ስያሜ እንዲሰጡ አድርጓቸዋል. ዲያና ቻርለስ ከካሚላ ጋር ያለውን ግንኙነት በአንድሪው ሞርተን፣ዲያና፣የእሷ እውነተኛ ታሪክ መጽሃፍ አጋልጧል። የራሷ የሆነ ከትዳር ውጪ ማሽኮርመም የሚያሳዩ የድምጽ ካሴቶችም ብቅ አሉ።ሂዊት የልዑል ሃሪ አባት ነው የሚለው የማያቋርጥ አስተያየት በሄዊት እና ሃሪ መካከል ባለው አካላዊ መመሳሰል ላይ ነው። ይሁን እንጂ ሃሪ የዲያና ከሄዊት ጋር የነበራት ግንኙነት በጀመረበት ጊዜ አስቀድሞ ተወለደ። ሕጋዊ መለያየት እና ፍቺ በታህሳስ 1992 የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆን ሜጀር የጥንዶቹን ህጋዊ መለያየት በፓርላማ አስታወቁ። በዚያው ዓመት መጀመሪያ ላይ የብሪቲሽ ፕሬስ እ.ኤ.አ. በ 1989 በቻርልስ እና ካሚላ መካከል የተደረገ ጥልቅ የሆነ የስልክ ውይይት ግልባጭ ታትሞ ነበር ፣ እሱም በፕሬስ ካሚልጌት የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። ልዑል ቻርለስ በሰኔ 29 ቀን 1994 በተለቀቀው ቻርልስ፡ የግል ሰው፣ የህዝብ ሚና፣ ከጆናታን ዲምብልቢ ጋር በተለቀቀው የቴሌቪዥን ፊልም ውስጥ የህዝብ ግንዛቤን ፈለገ። እ.ኤ.አ. በ 1986 ማህበራቸውን እንደገና ያቋቋሙት ከዲያና ጋር ካገባ በኋላ “በማይመለስ ፈርሷል” ። ቻርለስ እና ዲያና በነሐሴ 28 ቀን 1996 ተፋቱ። ዲያና በሚቀጥለው ዓመት ኦገስት 31 በፓሪስ በመኪና አደጋ ተገድላለች ። ቻርለስ ገላዋን ወደ ብሪታንያ ለመመለስ ከዲያና እህቶች ጋር ወደ ፓሪስ በረረ። ከካሚላ ፓርከር ቦልስ ጋር ጋብቻ የቻርለስ እና የካሚላ ፓርከር ቦልስ ተሳትፎ በየካቲት 10 ቀን 2005 ተገለጸ። ለአያቱ የሆነችውን የእጮኝነት ቀለበት አበረከተላት። ንግስት ለጋብቻ የሰጠችው ፍቃድ (በሮያል ጋብቻ ህግ 1772 በተጠየቀው መሰረት) በመጋቢት 2 በፕራይቪ ካውንስል ስብሰባ ላይ ተመዝግቧል። በካናዳ የፍትህ ዲፓርትመንት ለካናዳ የንግስት ፕራይቪ ካውንስል መገናኘቱ የማይጠበቅበት በመሆኑ ህብረቱ ዘር ስለማያገኝ እና በካናዳ ዙፋን ላይ ምንም አይነት ተጽእኖ ስለማይኖረው የፍትህ ዲፓርትመንት ውሳኔውን አሳውቋል። . ቻርልስ በእንግሊዝ ውስጥ ከቤተክርስቲያን ሰርግ ይልቅ የሲቪል ቤተሰብ የነበራቸው ብቸኛው የንጉሣዊ ቤተሰብ አባል ነበሩ። በ1950ዎቹ እና 1960ዎቹ በቢቢሲ የታተሙት የመንግስት ሰነዶች እንዲህ አይነት ጋብቻ ህገወጥ እንደሆነ ይገልፃሉ፣ ምንም እንኳን እነዚህ በቻርልስ ቃል አቀባይ ውድቅ የተደረጉ ቢሆንም በስልጣን ላይ ባለው መንግስት ጊዜ ያለፈባቸው መሆናቸውን ገልፀዋል ። ጋብቻው በዊንሶር ቤተመንግስት በተካሄደው የሲቪል ስነ ስርዓት እንዲፈፀም ታቅዶ የነበረ ሲሆን በመቀጠልም በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ሃይማኖታዊ ቡራኬ ተሰጥቷል። ቦታው በመቀጠል ወደ ዊንዘር ጊልዳል ተቀይሯል፣ ምክንያቱም በዊንዘር ቤተመንግስት የሚደረግ የሲቪል ጋብቻ ቦታው እዚያ ለመጋባት ለሚፈልግ ማንኛውም ሰው እንዲገኝ ስለሚያስገድድ ነው። ከሠርጉ አራት ቀናት በፊት ቻርልስ እና አንዳንድ የተጋበዙት ሹማምንቶች በርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ጆን ፖል ዳግማዊ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ እንዲገኙ ለማስቻል በመጀመሪያ ከታቀደለት ኤፕሪል 8 ቀን ጀምሮ እስከ ማግሥቱ ተላለፈ። የቻርለስ ወላጆች በሲቪል ጋብቻ ሥነ ሥርዓት ላይ አልተገኙም; ንግስቲቱ ለመገኘት ፈቃደኛ አለመሆን የእንግሊዝ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ገዥ ከመሆኗ የተነሳ ሊሆን ይችላል። የኤድንበርግ ንግሥት እና መስፍን የበረከት አገልግሎት ላይ ተገኝተዋል እና በኋላ በዊንሶር ቤተመንግስት አዲስ ተጋቢዎች አቀባበል አደረጉ። የካንተርበሪው ሊቀ ጳጳስ ሮዋን ዊልያምስ በዊንሶር ካስትል በሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎት ቤት በረከቱ በቴሌቭዥን ተላለፈ። በጎ አድራጎት እና በጎ አድራጎት እ.ኤ.አ. እነዚህ በአንድ ላይ፣ እራሱን እንደ “በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ትልቁ ባለ ብዙ-ምክንያት የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ በየዓመቱ ከ100 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ በማሰባሰብ የልኡል በጎ አድራጎት ድርጅት የሚባል የላላ ትብብር ይመሰርታል… ትምህርት እና ወጣቶች ፣ የአካባቢ ዘላቂነት ፣ የተገነባው አካባቢ ፣ ኃላፊነት የሚሰማው ንግድ እና ኢንተርፕራይዝ እና ዓለም አቀፍ። እ.ኤ.አ. በ 2010 ፣ የልዑል በጎ አድራጎት ካናዳ ከስሙ ጋር በተመሳሳይ መልኩ በእንግሊዝ ተመሠረተ። ቻርልስ ከ400 በላይ የሌሎች በጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ድርጅቶች ደጋፊ ነው። የካናዳ ጉብኝቱን ወጣቶችን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ አካባቢን፣ ስነ ጥበባትን፣ መድሀኒትን፣ አረጋውያንን፣ ቅርሶችን እና ትምህርትን ትኩረት ለመሳብ ለመርዳት እንደ መንገድ ይጠቀማል። በካናዳ ቻርልስ የሰብአዊ ፕሮጀክቶችን ደግፏል. ከሁለቱ ወንዶች ልጆቹ ጋር፣ እ.ኤ.አ. በ1998 የተከበረውን የዘር መድልዎ ለማስወገድ ዓለም አቀፍ ቀን በተከበሩ ስነ ሥርዓቶች ላይ ተሳትፏል። ቻርለስ በሜልበርን፣ ቪክቶሪያ ውስጥ የሚገኘውን የልዑል በጎ አድራጎት ድርጅት አውስትራሊያን አቋቁሟል። የልዑል በጎ አድራጎት ድርጅቶች አውስትራሊያ ለዌልስ ልዑል አውስትራሊያዊ እና ዓለም አቀፍ የበጎ አድራጎት ጥረቶች አስተባባሪነት ማቅረብ ነው። ቻርለስ የሮማኒያ አምባገነን ኒኮላ ሴውሼስኩ የሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳሳደረባቸው እና በአለም አቀፍ መድረክ ተቃውሞዎችን በማስነሳት እና በመቀጠልም የሮማኒያ ወላጅ አልባ ህጻናት እና የተጣሉ ህጻናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ፋውንዴሽን ደግፎ ከመጀመሪያዎቹ የአለም መሪዎች አንዱ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 2013 ቻርለስ ለብሪቲሽ ቀይ መስቀል የሶሪያ ቀውስ ይግባኝ እና በ 14 የብሪታንያ በጎ አድራጎት ድርጅቶች በሶሪያ የእርስ በርስ ጦርነት የተጎዱ ሰዎችን ለመርዳት ለሚያስተዳድሩት የብሪቲሽ ቀይ መስቀል የሶሪያ ቀውስ ይግባኝ እና የሶሪያ ይግባኝ መጠን ያልተገለጸ ገንዘብ ለግሷል። ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው፣ በ2013 ቻርልስ 65 አመቱ ካደረገ በኋላ የመንግስት ጡረታውን ለአረጋዊያን ድጋፍ ለሚሰጥ አንድ ስማቸው ላልታወቀ በጎ አድራጎት ድርጅት እንደለገሱ ይታመናል። በማርች 2014 ቻርለስ በደቡብ-ምስራቅ እስያ በኩፍኝ ወረርሽኝ በፊሊፒንስ ውስጥ ለአምስት ሚሊዮን የኩፍኝ-ኩፍኝ ክትባቶችን አዘጋጅቷል። ክላረንስ ሃውስ እንዳለው፣ ቻርለስ በ2013 ዮላንዳ በደረሰው ጉዳት ዜና ተጎድቶ ነበር።ከ2004 ጀምሮ ደጋፊ የሆነው አለም አቀፍ የጤና አጋሮች ክትባቱን ልከው ከአምስት አመት በታች የሆኑ አምስት ሚሊዮን ህጻናትን ይከላከላሉ ተብሎ ይታመናል። ከኩፍኝ በሽታ. በጃንዋሪ 2020 የዌልስ ልዑል ስደተኞችን እና በጦርነት፣ ስደት ወይም የተፈጥሮ አደጋ የተፈናቀሉ ሰዎችን ለመርዳት አላማ ያለው የአለምአቀፉ አድን ኮሚቴ የመጀመሪያው ብሪቲሽ ጠባቂ ሆነ። እ.ኤ.አ. በኤፕሪል 2021 እና በህንድ ውስጥ በኮቪድ-19 ጉዳዮች መስፋፋቱን ተከትሎ ቻርልስ መስራቹ በሆነው በብሪቲሽ እስያ ትረስት ህንድ ለድንገተኛ ይግባኝ መጀመሩን በማወጅ መግለጫ አውጥቷል። ይግባኝ፣ ኦክሲጅን ለህንድ ተብሎ የሚጠራው፣ ለተቸገሩ ሆስፒታሎች የኦክስጂን ማጎሪያዎችን በመግዛት ረድቷል። እ.ኤ.አ. በጥር 2022 ቻርልስ ሰባት አርቲስቶችን የሰባት እልቂት የተረፉ ሰዎችን ምስል እንዲሳሉ አዟል። ስዕሎቹ በቡኪንግሃም ቤተ መንግስት በሚገኘው የንግስት ጋለሪ እና በሆሊሪድ ሃውስ ቤተ መንግስት እንዲታዩ የተደረገ ሲሆን የተረፉት፡ የሆሎኮስት ምስሎች በሚል ርዕስ በቢቢሲ ሁለት ዘጋቢ ፊልም ላይ ይቀርባል። የተገነባ አካባቢ የዌልስ ልዑል በሥነ ሕንፃ እና በከተማ ፕላን ላይ ያለውን አመለካከት በግልፅ ገልጿል; የኒው ክላሲካል አርክቴክቸር እድገትን አሳደገ እና "እንደ አካባቢ፣ አርክቴክቸር፣ የውስጥ ከተማ እድሳት እና የህይወት ጥራት ባሉ ጉዳዮች ላይ በጥልቅ እንደሚያስብ" አስረግጦ ተናግሯል። እ.ኤ.አ. ሜይ 30 ቀን 1984 የብሪቲሽ አርክቴክቶች ሮያል ኢንስቲትዩት () 150ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ባደረጉት ንግግር በለንደን የሚገኘው ናሽናል ጋለሪ እንዲራዘም የታቀደውን “በጣም ተወዳጅ ጓደኛ ፊት ላይ ያለ አስፈሪ ካርበን” በማለት በሚያስታውስ ሁኔታ ገልፀዋል ። እና የዘመናዊ አርክቴክቸር "የመስታወት ግንዶች እና የኮንክሪት ማማዎች" ተቃወሙ። "የድሮ ህንፃዎችን፣ የመንገድ እቅዶችን እና ባህላዊ ሚዛኖችን ማክበር እና ለግንባታ ፣ ለጌጣጌጥ እና ለስላሳ ቁሳቁሶች ምርጫ የጥፋተኝነት ስሜት እንዳይሰማን በሰው ልጅ አንፃር አስፈላጊ ነው" በማለት የአካባቢውን ማህበረሰብ ተሳትፎ ጠይቋል። በሥነ ሕንፃ ምርጫዎች ውስጥ እና ጠየቀ- በንድፍ ውስጥ ስሜትን የሚገልጹ እነዚያ ኩርባዎች እና ቅስቶች ለምን ሊኖረን አይችልም? ምን ችግር አለባቸው? ለምንድነው ሁሉም ነገር አቀባዊ፣ ቀጥ ያለ፣ የማይታጠፍ፣ በትክክለኛ ማዕዘኖች ብቻ - እና የሚሰራ? የእሱ መጽሃፍ እና የቢቢሲ ዘጋቢ ፊልም ኤ ቪዥን ኦፍ ብሪታንያ በዘመናዊ አርክቴክቸር ላይም ትችት ነበረው እና በፕሬስ ውስጥ ትችት ቢሰነዘርበትም ለባህላዊ የከተማነት ፣የሰው ልጅ ሚዛን ፣የታሪካዊ ህንፃዎች እድሳት እና ዘላቂ ዲዛይን ዘመቻ ማድረጉን ቀጥሏል። ሁለቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶቹ ( እና በኋላም ወደ አንድ የበጎ አድራጎት ድርጅት የተዋሃዱ) አመለካከቶቹን ያስተዋውቁ ነበር፣ እና የፖውንድበሪ መንደር በዱቺ ኦፍ ኮርንዋል ባለቤትነት በሌዎን ማስተር ፕላን ላይ ተገንብቷል። ክሪየር በልዑል ቻርልስ መሪነት እና በፍልስፍናው መሠረት። እ.ኤ.አ. በ1996 በርካታ የሀገሪቱ ታሪካዊ የከተማ ማዕከሎችን ያለገደብ መውደሙን ቻርለስ ካናዳ ውስጥ ለተገነባው አካባቢ ብሔራዊ እምነት እንዲፈጠር ረድቷል። እ.ኤ.አ. በ2007 የካናዳ ፌዴራል በጀት በማፅደቅ የተተገበረውን በብሪታንያ ብሄራዊ እምነት ላይ የተመሰለ እምነትን ለመፍጠር ለካናዳ ቅርስ ዲፓርትመንት ዕርዳታውን ሰጥቷል። እ.ኤ.አ. በ 1999 ልዑሉ ለታሪካዊ ቦታዎች ጥበቃ ዘላቂ ቁርጠኝነት ላሳዩ የማዘጋጃ ቤት መንግስታት በ ቅርስ ካናዳ ፋውንዴሽን የተሸለመውን የዌልስ ልዑል ሽልማት የማዘጋጃ ቤት ቅርስ አመራር ሽልማትን ለመጠቀም ተስማምተዋል። ቻርልስ አሜሪካን እየጎበኘ እና ካትሪና ያስከተለውን ጉዳት ሲቃኝ እ.ኤ.አ. በ2005 የናሽናል ህንፃ ሙዚየም ቪንሰንት ስኩላሊ ሽልማትን በሥነ ሕንፃ ዙሪያ ላደረገው ጥረት ተቀበለ። በማዕበል የተጎዱ ማህበረሰቦችን መልሶ ለማቋቋም ከሽልማት ገንዘቡ 25,000 ዶላር ለግሷል። እ.ኤ.አ. ከ1997 ጀምሮ የዌልስ ልዑል ሮማኒያን ጎብኝቷል በኒኮላይ ሴውሼስኩ የኮሚኒስት አገዛዝ ዘመን የኦርቶዶክስ ገዳማትን እና የትራንስሊቫኒያ ሳክሰን መንደሮችን ውድመት ለማየት እና ለማጉላት ቻርልስ የሮማኒያ ጥበቃ እና ማደስ ድርጅት የ ጠባቂ ነው ፣ እና ገዝቷል ። ሮማኒያ ውስጥ ያለ ቤት። የታሪክ ምሁሩ ቶም ጋላገር እ.ኤ.አ. በ 2006 ሮማኒያ ሊቤራ በተባለው የሮማኒያ ጋዜጣ ላይ ቻርለስ በዚያች ሀገር በንጉሣውያን የሮማኒያ ዙፋን እንደተሰጣቸው ፅፈዋል ። ውድቅ ተደርጎበታል ተብሎ ቢነገርም ቡኪንግሃም ፓላስ ሪፖርቶቹን ውድቅ አድርጓል። ቻርልስ በተጨማሪም "ስለ ኢስላማዊ ጥበብ እና ስነ-ህንፃ ጥልቅ ግንዛቤ" ያለው እና በኦክስፎርድ እስላማዊ ጥናት ማእከል ውስጥ እስላማዊ እና ኦክስፎርድ የስነ-ህንፃ ቅጦችን የሚያጣምር ሕንፃ እና የአትክልት ስፍራ በመገንባት ላይ ተሳትፏል። ቻርለስ አልፎ አልፎ እንደ ዘመናዊነት እና ተግባራዊነት ባሉ የስነ-ህንፃ ቅጦች በሚጠቀሙ ፕሮጀክቶች ውስጥ ጣልቃ ገብቷል ። እ.ኤ.አ. በ 2009 ቻርልስ ለቼልሲ ባራክስ ጣቢያ አዘጋጆች ለኳታር ንጉሣዊ ቤተሰብ የሎርድ ሮጀርስ ዲዛይን ለጣቢያው “ተስማሚ ያልሆነ” የሚል ምልክት ሰጠ። በመቀጠል፣ ሮጀርስ ከፕሮጀክቱ ተወግደዋል እና የፕሪንስ ፋውንዴሽን ለተገነባው አካባቢ ሌላ አማራጭ እንዲያቀርብ ተሾመ። ሮጀርስ ልዑሉ የሮያል ኦፔራ ሃውስ እና ፓተርኖስተር አደባባይን ዲዛይኖቹን ለማገድ ጣልቃ ገብተዋል እና የቻርለስን ድርጊት “ስልጣን አላግባብ መጠቀም” እና “ሕገ መንግስታዊ ያልሆነ” ሲሉ አውግዘዋል። ሎርድ ፎስተር፣ ዛሃ ሃዲድ፣ ዣክ ሄርዞግ፣ ዣን ኑቬል፣ ሬንዞ ፒያኖ እና ፍራንክ ጊህሪ እና ሌሎችም የልዑሉ "የግል አስተያየቶች" እና "ከመጋረጃው በስተጀርባ ያለው ሎቢ" የ"ክፍት ስራውን" ለውጦታል ሲሉ ቅሬታቸውን ለሰንደይ ታይምስ ደብዳቤ ፃፉ። እና ዲሞክራሲያዊ እቅድ ሂደት ". ፒርስ ጎው እና ሌሎች አርክቴክቶች የቻርለስን አመለካከት እንደ “ኤሊቲስት” በማውገዝ ባልደረቦቻቸው በ2009 ቻርልስ ለ የሰጡትን ንግግር እንዲተዉ በሚያበረታታ ደብዳቤ ላይ አውግዘዋል። እ.ኤ.አ. በ 2010 የፕሪንስ ፋውንዴሽን ለተገነባው አካባቢ ዋና ከተማዋ በ2010 በሄይቲ የመሬት መንቀጥቀጥ ከተደመሰሰች በኋላ በፖርት-አው-ፕሪንስ ሄይቲ ውስጥ ያሉ ሕንፃዎችን እንደገና ለመገንባት እና ዲዛይን ለማድረግ ወሰነ። ፋውንዴሽኑ በካቡል፣ አፍጋኒስታን እና በኪንግስተን ጃማይካ የሚገኙ ታሪካዊ ሕንፃዎችን በማደስ ይታወቃል። ፕሮጀክቱ ለተገነባው አካባቢ የፕሪንስ ፋውንዴሽን "እስካሁን ትልቁ ፈተና" ተብሎ ተጠርቷል. ለኒው ክላሲካል አርክቴክቸር ጠባቂ ሆኖ ለሰራው ስራ፣ በ2012 የድሪሀውስ አርክቴክቸር ሽልማት ለቅኝት ተሸልሟል። በኖትር ዳም ዩኒቨርሲቲ የተሰጠው ሽልማት ለአዲስ ክላሲካል አርክቴክቸር እና የከተማ ፕላን ከፍተኛው የስነ-ህንፃ ሽልማት ተደርጎ ይወሰዳል። የጉበት ኩባንያ ቁርጠኝነት የአናጢዎች አምላኪ ኩባንያ ቻርለስን እንደ የክብር ሊቨርይማን የጫነው "ለለንደን አርክቴክቸር ያለውን ፍላጎት በማሳየት" ነው። የዌልስ ልዑል እንዲሁም የመርከብ ጸሐፊዎች የአምላኪ ኩባንያ ቋሚ መምህር፣ የድራፐርስ አምላኪ ኩባንያ ፍሪማን፣ የአምልኮ ሙዚቀኞች የክብር ፍሪማን፣ የወርቅ አንጥረኞች አምላኪ ኩባንያ ረዳት ፍርድ ቤት የክብር አባል፣ እና የአትክልተኞች አምላኪ ኩባንያ ሮያል ሊቨርይማን። የተፈጥሮ አካባቢ ከ1970ዎቹ ጀምሮ ቻርለስ የአካባቢ ግንዛቤን አስተዋውቋል። የካርቦን ዱካውን ለመቀነስ ባዮማስ ማሞቂያዎችን ተጠቅሟል , በተጨማሪም በንብረቱ አጠገብ ባለው ወንዝ ውስጥ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ተርባይን ተክሏል. በክላረንስ ሃውስ እና ሃይግሮቭ የፀሐይ ፓነሎችን ተጠቅሟል፣ እና በግዛቶቹ ላይ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ከመጠቀም በተጨማሪ - አስቶን ማርቲን 6 በ 85 ላይ ይሰራል። ወደ ሃይግሮቭ ሃውስ ሲዘዋወር ቻርልስ የኦርጋኒክ እርሻ ፍላጎትን አዳበረ፣ በ1990 የራሱን ኦርጋኒክ ብራንድ ይፋ ባደረገበት ወቅት፣ አሁን ከ200 በላይ የተለያዩ በዘላቂነት የሚመረቱ ምርቶችን ከምግብ እስከ የአትክልት ዕቃዎች ይሸጣል። ትርፉ (በ2010 ከ6 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ) ለልዑል በጎ አድራጎት ድርጅቶች ተሰጥቷል። በንብረቱ ላይ ሥራን በመመዝገብ፣ ቻርለስ በጋራ ፃፈ (ከቻርለስ ክሎቨር፣ የዴይሊ ቴሌግራፍ የአካባቢ ጥበቃ አርታኢ ጋር) ፡ በኦርጋኒክ አትክልትና እርሻ ላይ ያለ ሙከራ፣ በ1993 የታተመ እና ለጓሮ ኦርጋኒክ ደጋፊነቱን አቀረበ። በተመሳሳይ መልኩ የዌልስ ልዑል በእርሻ እና በውስጡ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች በመሳተፍ ከገበሬዎች ጋር በመገናኘት ስለ ንግድ ሥራቸው ይወያይ ነበር። ምንም እንኳን እ.ኤ.አ. በ 2001 በእንግሊዝ የተከሰተው የእግር እና የአፍ ወረርሽኝ ቻርለስ በሳስካችዋን የሚገኙ የኦርጋኒክ እርሻዎችን እንዳይጎበኝ ቢከለክለውም፣ በአሲኒቦያ ማዘጋጃ ቤት ከገበሬዎች ጋር ተገናኘ። በ2004፣ የብሪታንያ በግ ገበሬዎችን ለመደገፍ እና የበግ ስጋን የበለጠ ለማድረግ ያለመ የሙትን ህዳሴ ዘመቻን መሰረተ። ለብሪታንያውያን ማራኪ። የእሱ ኦርጋኒክ ግብርና የሚዲያ ትችቶችን ስቧል፡ ዘ ኢንዲፔንደንት በጥቅምት 2006 እንደገለጸው፣ "የዱቺ ኦርጅናል ታሪክ ስምምነትን እና ስነምግባርን የተላበሰ ነው፣ ከተወሰነ የሸቀጣሸቀጥ ፕሮግራም ጋር ተጋባ።" እ.ኤ.አ. በ2007 10ኛውን የአለም አቀፍ የአካባቢ ዜጋ ሽልማትን ከሃርቫርድ የህክምና ትምህርት ቤት የጤና እና የአለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ማእከል ተቀበለ ፣የዚህም ዳይሬክተር ኤሪክ ቺቪያን “ለአስርተ አመታት የዌልስ ልዑል የተፈጥሮ አለም ሻምፒዮን ሆኖ ቆይቷል። ... የኃይል ቆጣቢነትን ለማሻሻል እና በመሬት ላይ ፣ በአየር እና በውቅያኖሶች ውስጥ መርዛማ ንጥረ ነገሮችን በመቀነስ ረገድ በሚደረገው ጥረት የዓለም መሪ ሆኖ ቆይቷል። የቻርለስ የግል ጄት ጉዞ ከአውሮፕላን ደደብ ጆስ ጋርማን ትችት አስከትሏል። እ.ኤ.አ. በ2007፣ ቻርለስ የፕሪንስ ሜይ ዴይ ኔትወርክን ጀመረ፣ ይህም የንግድ ድርጅቶች በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ እንዲወስዱ የሚያበረታታ ነው። እ.ኤ.አ. ቀጥሎ በተካሄደው የጭብጨባ ጭብጨባ የዩናይትድ ኪንግደም የነፃነት ፓርቲ መሪ ኒጄል ፋራጅ ተቀምጠው የቻርልስ አማካሪዎችን “ከሁሉ ይልቅ ሞኞች እና ሞኞች” ሲሉ ገልፀዋቸዋል። እ.ኤ.አ. የካቲት 9 ቀን 2011 ቻርለስ በዝቅተኛ የካርቦን ብልጽግና ስብሰባ ላይ በአውሮፓ ፓርላማ ክፍል ውስጥ ባደረጉት ንግግር የአየር ንብረት ለውጥ ተጠራጣሪዎች ከፕላኔቷ የወደፊት ዕጣ ጋር "የማይረባ የ ጨዋታ" እየተጫወቱ ነው እናም በሕዝብ አስተያየት ላይ "የመበስበስ ውጤት" እያሳደሩ ነው ብለዋል ። በተጨማሪም የአሳ ሀብትን እና የአማዞን የዝናብ ደንን የመጠበቅ እና አነስተኛ የካርቦን ልቀትን በተመጣጣኝ ዋጋ እና ተወዳዳሪ ለማድረግ እንደሚያስፈልግ ተናግሯል።በ2011 ቻርልስ ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በነበረው ግንኙነት የሮያል ሶሳይቲ ለአእዋፍ ጥበቃ ሜዳሊያ ተቀበለ። የዝናብ ደኖች. እ.ኤ.አ. ኦገስት 27 ቀን 2012 የዌልስ ልዑል ለአለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ህብረት - የአለም ጥበቃ ኮንግረስ ንግግር አቅርበው የአፈር እና የሳር መሬትን ምርታማነት ለመጠበቅ የግጦሽ እንስሳት ያስፈልጋሉ የሚለውን አመለካከት በመደገፍ፡- በተለይ በዚምባብዌ እና በሌሎች ከፊል ደረቃማ አካባቢዎች አለን ሳቮሪ የተባለ አስደናቂ ሰው ለዓመታት ሲሟገት የቆየውን የሊቃውንት አመለካከት ከልቤ ግጦሽ የሚያሽከረክሩትን ቀላል የቀንድ ከብቶች በመቃወም በጣም አስደነቀኝ። ለም መሬት በረሃ ለመሆን። በተቃራኒው፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በሥዕላዊ መግለጫው እንዳሳየው፣ ዑደቱ እንዲጠናቀቅ መሬቱ የእንስሳት መኖ እና ፍሳሾቻቸው እንዲኖሩት ይፈልጋል፣ ስለዚህም የአፈርና የሣር ሜዳዎች ፍሬያማ እንዲሆኑ። ግጦሾችን ከመሬት ላይ ወስደህ ሰፊ በሆነ መኖ ውስጥ ብትቆልፋቸው ምድሪቱ ይሞታል። በፌብሩዋሪ 2014፣ ቻርልስ በክረምት ጎርፍ የተጎዱ ነዋሪዎችን ለማግኘት የሶመርሴትን ደረጃዎች ጎበኘ። በጉብኝቱ ወቅት ቻርልስ "ሰዎች አንድ ነገር ማድረግ እንዲጀምሩ ለማድረግ እንደ አስደሳች አደጋ ያለ ምንም ነገር የለም. አሳዛኝ ነገር ለረዥም ጊዜ ምንም ነገር አለመከሰቱ ነው." ቤተሰቦችን እና ንግዶችን ለመርዳት በልዑል ገጠራማ ፈንድ የተደገፈ £50,000 ድጋፍ ለመስጠት ቃል ገብቷል። እ.ኤ.አ. በታህሳስ 2015 ቻርለስ ለ 21 የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ንግግር አደረገ ፣ ለደን መጨፍጨፍ ምክንያት የሆኑትን ድርጊቶች እንዲያቆሙ ኢንዱስትሪዎች ተማጽነዋል። እ.ኤ.አ. በነሀሴ 2019 የዌልስ ልዑል ከብሪቲሽ ፋሽን ዲዛይነሮች ቪን እና ኦሚ ጋር በመተባበር በሀይግሮቭ እስቴት ውስጥ ከሚገኙ መረቦች የተሠሩ ልብሶችን ለማምረት ተባብሮ እንደነበር ተገለጸ። በተለምዶ "ምንም ዋጋ እንደሌላቸው የሚታሰቡ" የእፅዋት ዓይነት ናቸው. የሃይግሮቭ ተክል ቆሻሻ በአለባበስ የሚለብሱ ጌጣጌጦችን ለመፍጠርም ጥቅም ላይ ውሏል። በሴፕቴምበር 2020 የዌልስ ልዑል አጫጭር ፊልሞችን እና እንደ የአየር ንብረት ለውጥ እና ዘላቂነት ባሉ ጉዳዮች ላይ መጣጥፎችን የሚያሳይ የተባለ የመስመር ላይ መድረክን አስጀመረ። እሱ የመድረኩ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ያገለግላል። መድረኩ ከጊዜ በኋላ ከአማዞን ፕራይም ቪዲዮ እና ከዋተርቢር ጋር በመተባበር ለአካባቢያዊ ጉዳዮች የተለየ የዥረት መድረክ ፈጠረ።በዚያው ወር የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት ከማርሻል ፕላን ጋር የሚመሳሰል ወታደራዊ አይነት ምላሽ እንደሚያስፈልግ በንግግራቸው ተናግሯል። እ.ኤ.አ. በጥር 2020 ቻርስ በዳቮስ በተካሄደው የአለም ኢኮኖሚክ ፎረም አመታዊ ስብሰባ የዘላቂ ገበያዎች ተነሳሽነትን ጀምሯል፣ይህም ፕሮጀክት ዘላቂነትን በሁሉም ተግባራት መሃል ላይ ማድረግን የሚያበረታታ ነው። በግንቦት 2020 የዌልስ ልኡል የዘላቂ ገበያዎች ተነሳሽነት እና የአለም ኢኮኖሚ ፎረም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ የተከሰተውን አለማቀፋዊ የኢኮኖሚ ድቀት ተከትሎ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገትን ማሳደግን የሚመለከት ታላቁን ዳግም ማስጀመር ፕሮጀክት ባለ አምስት ነጥብ እቅድ ጀመሩ። እ.ኤ.አ. በጥር 2021 ቻርለስ ቴራ ካርታ ("ምድር ቻርተር")ን ዘላቂ የፋይናንስ ቻርተር ፈጠረ። እ.ኤ.አ. በጁላይ 2021 ቻርለስ እና ጆኒ ኢቭ ለአየር ንብረት ለውጥ እና ለአካባቢያዊ ጉዳዮች መፍትሄዎችን ለማግኘት በሮያል አርት ኮሌጅ የተፀነሰውን የቴራ ካርታ ዲዛይን ላብራቶሪ አስታወቁ ፣ አሸናፊዎቹ በገንዘብ የሚደገፉ እና ከዘላቂው የኢንዱስትሪ መሪዎች ጋር ያስተዋውቃሉ። የገበያ ተነሳሽነት። በሴፕቴምበር 2021 የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን ስለ ምግብ ስርዓት ለማስተማር እና የምግብ ብክነትን ለማስወገድ ያለመ ከጂሚ ዶሄርቲ እና ከጄሚ ኦሊቨር አስተዋፅዖ ያለው ፕሮግራምን ለወደፊት የምግብ ተነሳሽነት ጀምሯል። ቻርልስ የናሽናል ሄጅላይንግ ሶሳይቲ ጠባቂ ሆኖ በእንግሊዝ ውስጥ የተተከሉትን ቁጥቋጦዎችን ለመጠበቅ እንዲረዳው ሃይጅግሮቭ ስቴት ለድርጅቱ የገጠር ውድድር አቀባበል አድርጓል። በሰኔ 2021፣ በ47ኛው 7 የመሪዎች ጉባኤ ላይ በንግስቲቷ በተዘጋጀው የአቀባበል ስነ ስርዓት እና በ7 መሪዎች እና በዘላቂ ኢንዱስትሪያል ዋና ስራ አስፈፃሚዎች መካከል በተደረገው ስብሰባ ላይ መንግስታዊ እና ኮርፖሬት የአካባቢ ችግሮችን ለመፍታት ተሳትፈዋል። እ.ኤ.አ. በጥቅምት 2021 በ 2021 20 ሮም ስብሰባ ላይ ንግግር አድርጓል ፣ 26 የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ወደ አረንጓዴ መሪነት ዘላቂ ኢኮኖሚ የሚመራ እርምጃዎችን ለመጠየቅ “የመጨረሻው ዕድል ሳሎን” በማለት ገልፀዋል ።] በመክፈቻው ላይ ባደረጉት ንግግር የ 26 ሥነ-ስርዓት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም “የዓለምን የግሉ ሴክተር ጥንካሬ ለማዳበር” ሰፊ ወታደራዊ መሰል ዘመቻ እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ካለፈው ዓመት የተሰማውን ስሜት ደግሟል። እ.ኤ.አ. በ 2021 ልዑል ቻርልስ ስለ አካባቢው ለቢቢሲ ተናግረው በሳምንት ሁለት ቀን ሥጋም ሆነ አሳ አይበላም እና በሳምንት አንድ ቀን ምንም የወተት ተዋጽኦዎችን አይበላም ብለዋል ። አማራጭ ሕክምና ቻርለስ አማራጭ ሕክምናን አወዛጋቢ በሆነ መንገድ ደግፏል። የልዑል የተቀናጀ ጤና ድርጅት አጠቃላይ ሐኪሞች ከዕፅዋት የተቀመሙ መድኃኒቶችን እና ሌሎች አማራጭ ሕክምናዎችን ለብሔራዊ የጤና አገልግሎት ታካሚዎች እንዲያቀርቡ በሚያደርገው ዘመቻ ከሳይንሳዊ እና የህክምና ማህበረሰብ ተቃውሞ ስቧል እና በግንቦት 2006 ቻርልስ በጄኔቫ በተካሄደው የዓለም ጤና ስብሰባ ላይ ንግግር አደረገ ። የባህላዊ እና አማራጭ መድሃኒቶችን ማዋሃድ እና ስለ ሆሚዮፓቲ መሟገት. በኤፕሪል 2008 ዘ ታይምስ የፕሪንስ ፋውንዴሽን አማራጭ ሕክምናን የሚያስተዋውቁ ሁለት መመሪያዎችን እንዲያስታውስ የጠየቀውን የኤክሰተር ዩኒቨርሲቲ የተጨማሪ ሕክምና ፕሮፌሰር ኤድዛርድ ኤርነስት የጻፈው ደብዳቤ “አብዛኞቹ አማራጭ ሕክምናዎች ክሊኒካዊ ውጤት የሌላቸው ይመስላሉ፣ እና ብዙዎች አደገኛ ናቸው። የፋውንዴሽኑ አንድ ተናጋሪ ትችቱን በመቃወም እንዲህ በማለት ተናግሯል:- “የእኛ የመስመር ላይ ህትመቶች ማሟያ ጤና ጥበቃ፡መመሪያ ስለ ማሟያ ሕክምናዎች ጥቅሞች ምንም ዓይነት አሳሳች ወይም ትክክለኛ ያልሆነ የይገባኛል ጥያቄ ይዟል የሚለውን ውንጀላ ሙሉ በሙሉ አንቀበልም። ሰዎች አስተማማኝ የመረጃ ምንጮችን እንዲመለከቱ በማበረታታት ኃላፊነት የተሞላበት አካሄድ ... በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲያደርጉ ፋውንዴሽኑ ተጨማሪ ሕክምናዎችን አያበረታታም." በዛ አመት ኤርነስት ከሲሞን ሲንግ ጋር ለ"" በፌዝ የተጻፈ መጽሃፍ አሳተመ። የመጨረሻው ምዕራፍ የቻርለስ የተጨማሪ እና አማራጭ ሕክምናዎችን ጥብቅና የሚመለከት ነው። የፕሪንስ ዱቺ ኦርጅናሎች የተለያዩ ተጨማሪ የመድኃኒት ምርቶችን ያመርታሉ፣ ኤድዛርድ ኤርነስት “አደጋ ተጋላጭ የሆኑትን በገንዘብ መጠቀሚያ” እና “ቀጥተኛ መንቀጥቀጥ” በማለት ያወገዘው “”ን ጨምሮ። እ.ኤ.አ. በ2009 የማስታወቂያ ደረጃዎች ባለስልጣን ዱቺ ኦርጂናል የኢቺና-ረሊፍ፣ ሃይፐር ሊፍት እና ዲቶክስ ቲንክቸር ምርቶችን ለማስተዋወቅ የላከው ኢሜይል አሳሳች ነው ሲል ተችቷል። ልዑሉ እንደነዚህ ያሉትን ከዕፅዋት የተቀመሙ መድኃኒቶችን የሚመለከቱትን ደንቦች ከማቃለላቸው ጥቂት ቀደም ብሎ ለመድኃኒቶች እና የጤና እንክብካቤ ምርቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ () ቢያንስ ሰባት ደብዳቤዎችን ጽፈዋል ፣ ይህ እርምጃ በሳይንቲስቶች እና በሕክምና አካላት በሰፊው የተወገዘ ነው ። በጥቅምት 2009 ፣ በኤን ኤች ኤስ ውስጥ የበለጠ አማራጭ ሕክምናዎችን በተመለከተ ቻርልስ የጤና ፀሐፊውን አንዲ በርንሃምን በግል እንደጠየቀ ተዘግቧል። እ.ኤ.አ. በ 2016 ቻርልስ በንግግሩ ውስጥ በእርሻ ቦታው ውስጥ አንቲባዮቲክን ለመቀነስ የሆሚዮፓቲ የእንስሳት መድኃኒቶችን እንደተጠቀመ ተናግሯል ። በኤፕሪል 2010፣ የሂሳብ አያያዝ መዛባትን ተከትሎ፣ የፕሪንስ ፋውንዴሽን የቀድሞ ባለስልጣን እና ባለቤታቸው በአጠቃላይ £300,000 ነው ተብሎ በማጭበርበር ታሰሩ። ከአራት ቀናት በኋላ ፋውንዴሽኑ "የተቀናጀ ጤና አጠቃቀምን የማስተዋወቅ ቁልፍ አላማውን አሳክቷል" በማለት መዘጋቱን አስታውቋል። የበጎ አድራጎት ድርጅቱ የፋይናንስ ዳይሬክተር አካውንታንት ጆርጅ ግሬይ በአጠቃላይ 253,000 ፓውንድ የስርቆት ወንጀል ተከሶ የሶስት አመት እስራት ተፈርዶበታል። የፕሪንስ ፋውንዴሽን እንደገና ታጥቆ በ2010 የመድኃኒት ኮሌጅ ተብሎ እንደገና ተጀመረ። ሃይማኖታዊ እና ፍልስፍናዊ ፍላጎቶች ልዑል ቻርለስ በ16 አመቱ በካንተርበሪ ሊቀ ጳጳስ ሚካኤል ራምሴ በ1965 ፋሲካ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቻፕል ዊንዘር ቤተመንግስት ተረጋግጧል። በሃይግሮቭ አቅራቢያ በሚገኙ የተለያዩ የአንግሊካን ቤተክርስትያኖች ውስጥ አገልግሎቶችን ይከታተላል እና በባልሞራል ካስትል በሚቆይበት ጊዜ የስኮትላንድ ክራቲ ኪርክ ቤተክርስትያን ከተቀረው የንጉሣዊ ቤተሰብ ጋር ይሄዳል። እ.ኤ.አ. በ2000 የስኮትላንድ ቤተክርስቲያን አጠቃላይ ጉባኤ ጌታ ከፍተኛ ኮሚሽነር ሆኖ ተሾመ። ቻርለስ በአቶስ ተራራ ላይ እንዲሁም በሩማንያ ውስጥ የኦርቶዶክስ ገዳማትን (በአንዳንድ ሚስጥሮች መካከል) ጎበኘ። ቻርለስ በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የኦክስፎርድ እስላማዊ ጥናት ማዕከል ጠባቂ ሲሆን በ2000ዎቹም የከፍተኛ ትምህርት ማርክፊልድ ኢንስቲትዩት በብዙ መድብለ ባሕላዊ አውድ ውስጥ ለኢስላማዊ ጥናቶች የተዘጋጀውን መርቋል። ሰር ሎረንስ ቫን ደር ፖስት በ1977 የቻርልስ ጓደኛ ሆነ። እሱ “መንፈሳዊ ጉሩ” ተብሎ ተጠርቷል እና የቻርለስ ልጅ ልዑል ዊሊያም አባት ነበር። ከቫን ደር ፖስት ልዑል ቻርለስ በፍልስፍና እና በሌሎች ሃይማኖቶች ላይ ትኩረት አድርጓል። ቻርለስ በ2010 ሃርመኒ፡ አለምን የሚመለከት አዲስ መንገድ በተሰኘው መጽሃፉ የናውቲለስ መጽሃፍ ሽልማትን በማሸነፍ የፍልስፍና ሀሳቡን ገልጿል። እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 2016፣ የብሪታንያ የመጀመሪያው የሶሪያ ኦርቶዶክስ ካቴድራል ለመሆን በቅዱስ ቶማስ ካቴድራል፣ አክቶን መቀደስ ላይ ተገኝቷል። በጥቅምት 2019፣ በካርዲናል ኒውማን ቀኖና ላይ ተገኝተዋል። ቻርለስ እ.ኤ.አ. በጥር 2020 በኢየሩሳሌም የሚገኙትን የምስራቅ ቤተክርስቲያን መሪዎች ጎበኘ።በመጨረሻም በቤተልሔም በሚገኘው የልደታ ቤተክርስቲያን ውስጥ በተደረገው ኢኩሜኒካዊ አገልግሎት፣ከዚያም በኋላ በዚያች ከተማ ከክርስቲያን እና ከሙስሊም መኳንንት ጋር አልፏል። ምንም እንኳን ቻርለስ "የእምነት ተከላካይ" ወይም "የእምነት ተከላካይ" እንደ ንጉስ እንደሚሆን ቃል መግባቱ የተወራ ቢሆንም በ 2015 የንጉሱን ባህላዊ ማዕረግ "የእምነት ተከላካይ" እንደሚይዝ ገልጿል, "ይህን ግን ያረጋግጣል. የሌሎች ሰዎችን እምነት መለማመድ ይቻላል” ሲል የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ግዴታ አድርጎ ይመለከተዋል። ርዕሶች፣ ቅጦች፣ ክብር እና ክንዶች ርዕሶች እና ቅጦች ቻርለስ በህይወት ዘመናቸው ሁሉ የማዕረግ ስሞችን ይዟል፡ የንጉሣዊው የልጅ ልጅ፣ የንጉሣዊው ልጅ እና በራሱ መብት። ከተወለደ ጀምሮ የእንግሊዝ ልዑል ሲሆን በ1958 የዌልስ ልዑል ተፈጠረ። ልዑሉ በዙፋኑ ላይ ሲሾሙ የትኛውን የግዛት ስም እንደሚመርጡ ግምቶች ነበሩ። የመጀመሪያ ስሙን ከተጠቀመ, ቻርለስ በመባል ይታወቃል. ነገር ግን፣ ቻርልስ ለእናት አያቱ ክብር ሲል ጆርጅ ሰባተኛ ሆኖ ለመንገስ እንዲመርጥ እና ከስቱዋርት ነገሥታት 1ኛ ቻርልስ (አንገቱ የተቆረጠ) እና ቻርልስ (በእርሳቸው ከሚታወቀው) ጋር ግንኙነት እንዳይፈጠር ሐሳብ ማቅረቡን በ2005 ተዘግቧል። ዝሙት የበዛበት የአኗኗር ዘይቤ)፣ እንዲሁም በአንድ ወቅት የእንግሊዝና የስኮትላንድ ዙፋን ላይ ስቱዋርት አስመሳይ ቦኒ ልዑል ቻርሊን ለማስታወስ ንቁ መሆን፣ በደጋፊዎቹ “ቻርልስ ” ተብሎ ይጠራ ነበር። የቻርለስ ቢሮ "ምንም ውሳኔ አልተደረገም" ሲል ምላሽ ሰጥቷል. ክብር እና ወታደራዊ ሹመት እ.ኤ.አ. በ1972 ቻርልስ በሮያል አየር ሀይል ውስጥ የበረራ ሀላፊነት ከተሾመበት ጊዜ ጀምሮ በበርካታ ሀገራት የጦር ሃይሎች ውስጥ ጉልህ ደረጃዎችን አግኝቷል። ቻርልስ በጦር ኃይሎች ውስጥ የመጀመሪያ የክብር ሹመት የዌልስ ሮያል ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ሆኖ ነበር። በ1969 ዓ.ም. ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ልዑሉ እንደ ኮሎኔል-ዋና ኮሎኔል ፣ ኮሎኔል ፣ የክብር አየር ኮምሞዶር ፣ ኤር ኮምሞዶር-ዋና ፣ ምክትል ኮሎኔል-ዋና ፣ የሮያል የክብር ኮሎኔል ፣ ሮያል ኮሎኔል እና የክብር ኮሞዶር ቢያንስ 32 ተሹመዋል ። በብሪቲሽ ጦር ውስጥ ብቸኛው የውጭ ክፍለ ጦር የሆነው የሮያል ጉርካ ጠመንጃን ጨምሮ በኮመንዌልዝ ወታደራዊ አደረጃጀቶች። እ.ኤ.አ. ከ 2009 ጀምሮ ቻርለስ በካናዳ ጦር ኃይሎች በሶስቱም ቅርንጫፎች ሁለተኛ ደረጃን ይይዛል እና እ.ኤ.አ. ሰኔ 16 ቀን 2012 ንግስቲቱ በብሪቲሽ ጦር ኃይሎች ሶስት ቅርንጫፎች ውስጥ የዌልስ ልዑልን የክብር አምስት ኮከብ ማዕረግ ሰጠች ። በዋና አዛዥነት ሚናዋ ድጋፉ፣ የፍሊት አድሚራል፣ ፊልድ ማርሻል እና የሮያል አየር ሀይል ማርሻል አድርጎ ሾመው። በሰባት ቅደም ተከተሎች ተመርጦ ስምንት ጌጣጌጦችን ከኮመንዌልዝ ግዛቶች ተቀብሏል እና 20 የተለያዩ የክብር ሽልማቶችን ከውጭ መንግስታት እንዲሁም በዩናይትድ ኪንግደም, አውስትራሊያ እና ኒውዝላንድ ዩኒቨርሲቲዎች ዘጠኝ የክብር ዲግሪዎችን አግኝቷል. ልዑሉ የሚጠቀሙባቸው ባነሮች እንደየአካባቢው ይለያያሉ። የእሱ የግል ስታንዳርድ የዩናይትድ ኪንግደም ሮያል ስታንዳርድ ነው እንደ እጆቹ ልዩነት ባለ ሶስት ነጥብ አርጀንቲና እና በመሃል ላይ የዌልስ ርእሰ መስተዳደር ክንዶች መለያ። ከዌልስ፣ ከስኮትላንድ፣ ከኮርንዋል እና ከካናዳ ውጭ እና በመላው ዩናይትድ ኪንግደም ልዑሉ ከዩናይትድ ኪንግደም ጦር ኃይሎች ጋር በተገናኘ በይፋ በሚሰራበት ጊዜ ጥቅም ላይ ይውላል። በዌልስ ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውለው የግል ባንዲራ የተመሰረተው በዌልስ ሮያል ባጅ (የጊዊኔድ መንግሥት ታሪካዊ ክንዶች) ነው፣ እሱም አራት አራት ማዕዘኖችን ያቀፈ፣ የመጀመሪያው እና አራተኛው በወርቅ ሜዳ ላይ ከቀይ አንበሳ ጋር፣ እና ሁለተኛው እና ሶስተኛው በቀይ ሜዳ ላይ ከወርቅ አንበሳ ጋር. የዌልስ ልዑል ባለ አንድ-ቅስት ኮሮኔት ያለው ነው። በስኮትላንድ ከ 1974 ጀምሮ ጥቅም ላይ የዋለው የግል ባነር በሶስት ጥንታዊ የስኮትላንድ ማዕረጎች ላይ የተመሰረተ ነው-ዱክ ኦፍ ሮቴሳይ (የስኮትላንድ ንጉስ ወራሽ) ፣ የስኮትላንድ ከፍተኛ መጋቢ እና የደሴቶች ጌታ። ባንዲራ እንደ የአፕይን ክላን ስቴዋርት አለቃ ክንዶች በአራት አራት ማዕዘኖች የተከፈለ ነው። የመጀመሪያው እና አራተኛው አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው የወርቅ መስክ በሰማያዊ እና በብር የተሸፈነ ባንድ በመሃል ላይ; ሁለተኛውና ሦስተኛው አራተኛው ክፍል በብር ሜዳ ላይ ጥቁር ጋለሪ ያሳያል. ክንዶቹ ከአፒን የሚለያዩት በስኮትላንድ የተንሰራፋውን የተጨማለቀ አንበሳ የተሸከመ ኢንስኩትቼን በመጨመር ነው። ባለ ወራሹን ለማመልከት ባለ ሶስት ነጥብ ግልጽ መለያ የተበላሸ። በኮርንዋል፣ ባነር የኮርንዋል መስፍን ክንዶች ነው፡- “”፣ ማለትም፣ 15 የወርቅ ሳንቲሞች የያዘ ጥቁር ሜዳ። እ.ኤ.አ. በ 2011 የካናዳ ሄራልዲክ ባለስልጣን ለዌልስ ልዑል በካናዳ ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውል የግል ሄራልዲክ ባነር አስተዋወቀ ፣ የካናዳ ክንዶች ጋሻ በሁለቱም የዌልስ ልዑል ላባ በወርቅ የሜፕል አክሊል የተከበበ ሰማያዊ ክብ ቅርጽ ያለው ቅጠሎች, እና የሶስት ነጥብ ነጭ መለያ.
13700
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%8B%AE%E1%89%A5%20%E1%88%98%E1%8A%AE%E1%8A%95%E1%8A%95
እዮብ መኮንን
እዮብ መኮንን፣ ኢትዮጵያዊ ታዋቂ ዘፋኝ የነበረ ሲሆን ብዙ ዘመናዊ የሙዚቃ ስራዎችን አቅርቧል። ከነዚህም ዉስጥ ለኢትዮጵያ የሬጌ ሙዚቃ እድገት አስተዋፆ ያደረገበት ስሙን በጉልህ ያስጠራዋል። እዮብ መኮንን ባደረበት ድንገተኛ ህመም፣ በናይሮቢ ከተማ ሕክምናውን በሚከታተልበት ሆስፒታል እሁድ ማታ ነሐሴ ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. አርፏል። የህይወት ታሪክ እዮብ መኮንን እባላለሁ በነገራችን ላይ የወታደር ልጅ ነኝ አባቴ ወታደር እንደመሆኑ ከሀገር ሀገር በመዘዋወር ነበር ሀገሩን ያገለግል የነበረው ይኸው ሥራው ደግሞ ጂግጂጋ አድርሶት ከእናቴ ከአማረች ተፈራ የምሩ ጋር ለመተዋወቅ በቃና ጥቅምት 2 ቀን 1967 ዓም በጭናቅሰን ገብርኤል ጂግጂጋ ከተማ እኔ ተወለድኩ ዕድሜዬ ለትምህርት እንደደረሰም የአንደኛ ደረጃ ትምህርቴን በጂግጂጋ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከፈል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን ደግሞ ከአባቱ ከመኮንን ዘውዴ ይመኑ ጋር ወደ አስመራ በመሄድ የተከታተልኩ ሲሆን ቀሪውን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን ደግሞ ወደ ጂግጂጋ በመመለስ ተከታትያለሁ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን እየተከታተልኩ የሙዚቃ ፍቅር የገባቸው እና ሙዚቃን ከኔ በተሻለ ከሚሠሩ ልጆች ጋር በአቅራቢያዬ እየሄድኩ እለማመድ ጀመር ነገር ግን ለሙዚቃው አዲስ እንደመሆኔ መጠን በሙዚቃ መሣሪያ ከሚለማመዱት ልጆች ጋር እኩል ሙዚቃን መለማመድ አዳጋች ሆኖብኝ ነበር ይህንንም ለአብሮ አደግ ጓደኛዬ ሙዚቃን እየተለማመድኩ እንደሆነ እና ነገር ግን ከመሳሪያው እኩል ስጫወት ልከ እንደማይመጣልኝ እና መሣሪያው የሚያወጣው ድምፅም እንደሚረብሸኝ ስነግራት እሷም ግዴለህም እዮብ መዝፈን እንደምትችል እኔ በደንብ አውቃለሁ አንድ ቦታ ልውሰድህ አለችኝ እኔም እሺ ስላት በማግስቱ ሙዚቃን በተሻለ መልኩ የሚለማመዱ ሊጆች ጋር ይዛኝ ሄዳ አስተዋወቀችኝ። በሰዓቱ ስለ ሪትም ፣ ፒች ወዘተ የማውቀው ነገር አልነበረም ይህን ሁሉ ሳላውቅ ልጆቹ በሚለማመዱበት ቦታ ላይ ተገኘሁና በል ዝፈን ተባልኩ እኔም የቦብ ማርሊን ኖ ውመን ኖ ከራይ የሚለውን ዘፈን ሳንቆረቁርላቸው በጣም ወደዱኝ እና በዚያው አብሬያቸው እንድለማመድ ፈቀዱልኝ የሚጨመረውን ጨምሬ የሚቀነሰውንም ቀንሼ ከቀናት ልምምድ በኋላ መድረክ ላይ ይዘውኝ ወጡ መድረክ ላይ በወጣሁ የመጀመሪያው ቀን ሕዝቡ ተሸከሞኝ አብሮኝ ሲደሰት ዋለ። ያኔ መዝፈን እንደምችል ገባኝ በዚህ ጊዜ ከሙዚቃው ጎን ለጎን ራሴንም ሆነ ቤተሰቦቼን የምረዳው ከቦታ ቦታ እየተዘዋወርኩኝ በማነሳቸው ፎቶግራፎች አማካኝነት ነበር ፎቶ ግራፎቼን ለማሳጠብ ሐረር በምሄድበት ጊዜ ናሽናል የተባለ ሆቲል እየተጋበዝኩ እዘፍን ነበር። በዘፈንኩ ቁጥር ደግሞ ሽልማቱ በሽ በሽ ነው:: በዚህ ወቅት አሸናፊ ከበደ እነ ታምራት ደስታን ይዞ ጂግጃጋ መጣ እኔም ገና እንዳየኋቸው ዝም ብሎ ደስ አለኝ። መዝፈን መቻሌን ማወቁ ለዘፋኞች ልዩ ፍቅር እንዲኖረኝ አድርጎኛል። አዲስ አበባ ገብቶ የመዝፈን ጉጉቴም ከፍተኛ ስለነበር መዝፈን እንደምችል ነገርኳቸው እና አዲስ አበባ ይዛችሁኝ ካልሄዳችሁ ብዬ ለመንኳቸው እነሱ ግን አንተ እዚህ ጥሩ ኑሮ ነው ያለህ እዚያ ሄደህ ምን ታደርጋለህ ብለው መከሩኝ። እኔም ግዴላችሁም አላሳፍራችሁም ውሰዱኝ ብዬ ደጋግሜ ለመንኳቸው ነገር ግን ሁኔታዬ ስላላማራቸው ሥራቸውን ሠርተው ከጨረሱ በኋላ ጥለውኝ ጉዟቸውን ቀጠሉ። በዛው ሰሞን (1991 ዓ.ም) ሐረር ያነሳኋቸውን ፎቶግራፎች እያሳጠብኩ አብሮኝ ፎቶ ግራፍ ያነሳ የነበረን አንድ ልጅ ድንገት አገኘሁት (ስሙን ባልጠቅሰው ይሻላል) ያ ልጅ ሥራው አልሆንልህ ብሎት ከስሮ በነበረ ጊዜ እኔ ፎቶ ካሜራ ሰጥቼው ነው እንደገና ሥራ ያስጀመርኩት። ከልጁ ጋ እንደተገናኘን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ወሬ ስንጀምር መሻሻሉን እና ጉርሱም የምትባል ሀገር ፎቶ ቤት መከፈቱን ነግሮኝ እንደውም እዛ ከአዲስ አበባ የመጡ ዘፋኞች ሙዚቃ እያቀረቡ ስለሆነ ለምን አንሄድም አለኝ፡ በወቅቱ ኪሴ ውስጥ ሁለት ብር ብቻ ነው የነበረኝ እና ብር እንዳልያዝኩ ስነግረው አንተ ባለውለታዬ ነህ እኔ ሁሉንም ነገር እችልሀለሁ አለኝና ተያይዘን በሀይሉከስ ተጭነን ጉርሱም ገባን። እዚያ ስንደርስ አሁንም እነ አሸናፊ ከበደ ሙዚቃ እያቀረቡ ነው። በድጋሚ ሳገኛቸው ደስ ብሎኝ በድፍረት አስዘፍኑኝ አልኳቸው፡፡ እነሱም በመገረም አዩኝና እዚህም መጣህ አሉኝ እኔም አዎ አልኳቸው እና በድጋሚ እንዳ ዘፍኑኝ ለመንኳቸው እነሱም እሺ አሉና ዕድሉን ሰጥተውኝ መድረክ ላይ ወጥቼ ስዘፍን በሽልማት ተንበሸበሽኩ። እነ አሸናፊም ይህን ሲያዩ እሺ አዲስ አበባ ብንወስድህ ማን ጋር ታርፋለህ አሉኝ እኔም ካዛንቺስ አክስት ስላለችኝ እሷ ጋር ማረፍ እንደምችል ስነግራቸው ተስማሙና ይዘውኝ ጉዞአቸውን ቀጠሉ። እነሱ በየደረሱበት ሀገር አብሬ እየዘፈንኩ እና ፎቶ እያነሳሁ ከብዙ ቀናት ጉዞ በኋላ በ24 ዓመቴ አዲስ አበባ ገባሁ። አዲስ አበባ ካዛንቺስ አካባቢ አክስቴ ጋር ባረፍኩበት ወቅት የሀይልዬ ታደሰ ይሞታል ወይ የሚለው አልበሙ አዲስ ስለነበር በየጉራንጉሩ ሁሉ ይደመጥ ነበር። አዲስ አበባ በገባው በነጋታው አክስቴ ከኃይልዬ ጋር ትግባባ ስለነበር እሱ ናይት ክለብ እንድሠራ እንድታስፈቅድልኝ ስጠይቃት ያለምንም ማንገራገር ክለቡ ድረስ ሄዳ ስለእኔ ነገረችው። በነጋታው ኃይልዬ አስጠራኝና መዝፈን ትችላለህ አለኝ እኔም በደንብ እንደምችል እርግጠኛ ሆኜ ነገርኩት እሱም እንድሞከር እድሉን ሰጠኝ። ቀደም ሲል እንደገለፅከት ስለ ሪትም አጠባበቅና ስለሌላውም ነገር ምንም እውቀት ስለሌለኝ ገና ኪቦርድ ሲከፈት አብሬ መጮህ ስጀምር ይሄ ገና ይቀረዋል ብለው ገሸሽ አደረጉኝ እኔም የመገለል ስሜት ተሰምቶኝ ወጣሁና እዛ ቤት ዳግመኛ ሳልሄድ ቀረሁ። ለተወሰኑ ቀናት እቤት ቁጭ ብዬ እያንጎራጎርኩ ማንን ልጠይቅ ማንን ላናግር ማን ያዘፍነኝ በሚል ሀሳብ ተወጠርኩ ሌሎች የከለብ ባለቤቶችን ፈልጌ ማናገር እንዳለብኝ ራሴን አሳመንኩት ነገር ግን አንድ ምሽት ላይ የኔን ህይወት የሚቀይር ከስተት ተከሰተ በዛች የተባረከች ምሽት ፋልከን ክለብ ውስጥ ብዙ የውጭ ሀገር ዜጎች ሊዝናኑ ስለመጡ እንግሊዝኛ ዘፈን የግድ አስፈላጊ ስለነበር ተጠራሁ ጆሮዬን ባለማመን በፍጥነት ከተኛሁ ተነስቼ ወደ ክለቡ በመሄድ ጃምቦ ፋና የሚለወንና ሌሎች የአፍሪካ አ እንግሊዝኛ ዘፈኖችን እየሰባበርኩ አስነካሁት ከዛ ምሽት በኋላ ይሄ ለ ጎበዝ ነው ተባልኩና በወቅቱ የሀይልዬ ታደሰ ማናጀር በነበረው ወንድ አማካኝነት በደመወዝ ተቀጠርኩ፡ ከዛች ቀን በኋላ ኦሮሚኛውን ሱማሊኛውን፤ እንግሊዝኛወን የተጠየኩትን ቋንቋ ሁሉ እየሰባበርኩ መጫወት ጀመርኩ። ሰው እየወደደኝና አየተቀበለኝ ሄደ። እንደ አጋጣሚ የአከስቴም ቤት ፋልከ ከለብ አጠገበ ስለነበር ኑሮዬን አክስቴም ጋር ፋልከን ከለብ ውስጥም በማድረግ የአዲስ አበባን ኑሮ ተያያዝኩት። በ991 ዓ.ም ሙዚቃን እንደ ፕሮፌሽን ሀ ብዬ ፋልከን ከለብ ውስጥ በስፋት መጫወት ጀመርኩኝ በከለብ ህይወቴም በዋነኝነት የአሊ ቢራና የቦብ ማርሌን ዘፈኖች በስፋት አቀነቅን ነበር። ኦሮሚኛ መስማት እና መናገር ስለምችል ነው መሰለኝ ከሀገር ወስጥ ድምፃውያኖች ለአሊ ቢራ ልዩ ፍቅር አለኝ፡ የአሊ ቢራን ዘፈኖች ህፃን ሆኜ ወደ ትምህርት ቤት ስሄድ እያንጎራጎርኳቸው ስለምሄድ ልክ እንደ ህዝብ መዝሙር ሸምድጃቸው ነበር። ለብዙዎቹ የሀገራችን አርቲስቶች ፍቅር አ ክብር አለኝ ለባህል እና ሀገራዊ ሙዚቃዎች ግን ጌቴ አንለይን የመጀመሪያው ረድፍ ላይ ነው የማስቀምጠው ለሱ ልዩ ፍቅር አለኝ የቃላት አጠቃቀሙ ጉልበቱ የድምፁ ወብት ይማርከኛል። በተለይ ሀገሬን ስለምወድ ነው መሰለኝ ምናለኝ ሀገሬን በተለየ ሁኔታ እወዳታለሁ። ከዛ ውጪ ግን ብዙ ጊዜ መጽሀፍ ቅዱስ ማንበብ ያስደስተኛል። ልከ እንደ አሊ ቢራ ሁሉ ቦብም ሮል ሞዴሌ ነው። ቦብ ማርሌ ማለት ገላጭ ዘፋኝ ነው። ከቦብ በዜማ እንዴት ስሜት እንደሚገለፅ በደንብ ተምሬአለሁ። ቦብ ዜማን ከግጥሙ ጋር አብሮ ሲተርከው ከትርነቱ ቦታ ላይ ነው ቀጥታ በመንፈስ የሚወስደኝ። ቦብ ሲዘፍን ትንፋሽ አወሳሰዱ በስሜቱ ማዘኑን እና መቆጣቱን መግለፅ የሚችል ትልቅ ድምፃዊ ነው። እኔም እነዚህን ቴከኒኮች ከቦብ ማርሌይ የወረስኩት ይመስለኛል። ልክ እንደቦብ ማርሊ የሬጌን ዘፈኖች በደንብ ስለምጫወት እና ፀጉሬም ወደ ቦብ ይሄድ ስለነበር አድናቂዎቹ እና የሰፈር ልጆች ቦብ ብለው ነበር የሚጠሩኝ። መረጃውን ያጋራዋችሁ የአብስራ አለሙ ነኝ ለበለጠ መረጃ በቴሌግራም @ ላይ ያግኙኝ አምላክ ነብስህን በገነት ያኑርልን ኢዮባችን የስራ ዝርዝር >የፍቅር አኩኩሉ(ሲንግል) የመጀመሪያ አልበሙ "እንደ ቃል" >ያየሽውን አይቻለሁ >ግን በምን በለጥሻቸው >ደስተኛ ነኝ ከ ዘሪቱ ከበደ >ታሚኛለሽ አሉ >ወኪል ነሽ >ውል አይፃፍ >ነገን ላየው ሁለተኛው አልበሙ የአልበሙ መጠሪያ "እሮጣለሁ" ሲሆን በውስጡ 14 ሙዚቃወችን የያዘ ነው ሰማኋቸው *ትክክል ነሽ *ተጠርቸ *የጋበዝኳቸው *(አፋርኛ) *ወደናቴ ቤት *ማን ያውቃል ተው ያልሽኝን ተውኩት *አንደበቴ *ሳይ *ይለፍ *ዝም እላለሁ *እንዴት ብየ የኢትዮጵያ ዘፋኞች
3335
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8E%E1%8A%95%E1%8B%B0%E1%88%AD%20%E1%8A%A8%E1%89%B0%E1%88%9B
ጎንደር ከተማ
የጎንደር ከተማ ታሪክ ጎንደር ከ1628 ዓ ም ጀምሮ ለ200 ዓመታት የአፄወች መናገሻ በመሆኗ የምትታወቅ የዓለም ታዋቂ የታሪክ ተመራማሪወችን የምትስብ ውብ ከተማ ናት። የዘመኑ አፄዎች የገነቧቸው ቤተ መንግስቶችና አብያተ ክርስቲያናት (ፋሲል ግንብ፣ የጉዝራ፣ ጎመንጌ- አዘዞ ገነተ እየሱስ፣ ጎርጎራ ማንዴ ወዘተ) የከተማዋንና የኢትዮጵያን ታሪክ ለዓለም ጥሩ ገፅታ ለመሆናቸው ከተለያዩ ክፍለዓለማት እንደ ጎርፍ ለጉብኝትና ታሪክን ለመቃኘት የሚተመውን ለአብነት መጥቀሳችን ሁላችንም ያስማማናል። ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ከወረረ በኋላ የኢትዮጵያ ሕዝብ በአርበኝነት በረሀ ሲወርድ ያኔ ነበር የጣሊያን ወራሪው ሀይል ሕዝብን በማፈናቀል መሬትን መንጠቅ የጀመረው () ። ለአብነት የጎንደር ሲኒማ ቤት በፋሽስት ጣሊያን ከመሰራቱ በፊት እርስትነቱ የአቶ መንክር ተገኘ የተሰኙ በዚያን ዘመን ጎንደር ከተማ ውስጥ በጣም የላቁና የመጠቁ ነገረ ፈጅ ወይንም ጠበቃ ነበሩ። በዚያን ዘመን የህግ ባለሙያ ወይንም ጠበቃ ነበር ወይ ለምትሉ? በሀገራችን በዘመናዊ ትምህርት ቤት ባይማሩም ከቤተክህነት ትምህርትን የቀሰሙና ጥሩ አንደበተ ርህቱ የሆኑ ሰወች በጠበቃነት ተሰማርተው ይሰሩ ነበር። ይህ ደግሞ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ቀደምት ጥንታዊ ግሪካዊያንም በድሮ ዘመን የአቴንስ ጸሐፊዎችና ጥሩ ተናጋሪወች በጠበቃነት ያገለግሉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያመለክታሉ ። ጎንደርም አቶ መንክር ተገኘ ስመ ጥር ጠበቃ እንደነበሩ የከተማዋ ታሪክ አዋቂወች ይናገራሉ። በጣሊያን ወረራ ጊዜም አንዳድ የአካባቢው ነዋሪወችም አርበኞችን በማሳፈንና በማስገደል ከጣሊያን ጎን የቆሙትን ባንዳ ተብለው እንደሚጠሩ ታሪክ ያወሳል። ወደ ተነሳንበት ጉዳይ እንመለስና ጣሊያን ጎንደርን ማዕከል ለማድረግ በማለም በከተማዋ ውስጥ 352 ዛሬ የምናያቸውና ጣሊያን የሰራቸው ብለን የምንጠራቸውን ህንፃወችን ገነባ። እነኝህ ህንፃወች በአብላጫው ፒያሳ፣ጨዋ ሰፈር፣ አራተኛ ፎቅ፣ ቀበሌ 21 እንዲሁም የድሮው አገር አስተዳደርና ክፍተኛ ፍርድ ቤት አሁንም ግልጋሎት የሚሰጡትን እናያለን። ፒያሳን የንግድ መደብሮች፣የመዝናኛ ካፌና ፓርክ፣ሲኒማ ቤቱንና ባሩ፣ ምግብ ቤቶች ጣሊያኖች ለወታደሮቻቸውና ለጣሊያን ሲቪሊያን መገልገያ መመስረታቸውና ግልጋሎትም እነደሰጡ የሚጠቁሙት የአሁኑን 1- ቋራ ሆቴል በድሮ አጠራሩ () ሲመሰርቱ፣ 2- ጣሊያኖች አሊቤሮጎ ቻው ጣሊያን ሲወጣ እቴጌ መነን በኋላ ደግሞ ተራራ ሆቴል የተባለውን ያስታውሰናል። ሌላው ፒያሳወች ስንቆፋፍር አንድ ያገኘነው መረጃ ቅዱስ ዮሀንስ የድሮው የጎንደር ፓሊስ ማስልጠኛ ወደ ልደታ አካባቢ ሮም ጣሊያን ድረስ የሚሰማ የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ከጎንደር ተነቅሎ ወደ ሱዳን የሄደውና ኡምንድሩማን ሬዲዮ በመባል ካርቱም ላይ ግልጋሎት የሚሰጠው ከጎንደር የተሰረቀ እንደሆነ መረጃወች አሉ። –ወደ ኦቶ ባሮኮ መውረጃ ቅዱስ ገብረዓል ጋራጅ ወይንም ዮሴፍ ጋራጅ በመባል የሚታወቀው ደግሞ የጣሊያኖች የጦር አዛዥ መኖሪያ እንደነበርም ለማወቅ ችለናል። — ጣሊያን ከወጣ በኋላ የአሁኑን ቋራ ሆቴል አቶ ጌጡ ልዋጥህ የሚባለውን ወደ ልዑል መኮንን ሆቴል ብለው ቀይረው ግልጋሎት ይሰጡ ነበር –ጣሊያን ከለቀቀ ማግስት ን በማደስ እቴጌ መነን ሆቴል ()ይመልከቱ ብለው እንደገና የከፈቱት የጃንሆይ ልጅ ልዕል ተናኘ ወርቅና ቡስኪ የተባለ ጣሊያን በጋራ ነበር በኋላም ተራራ ሆቴል ተብሎ መንግስት የወረሰው –ጣሊያን ከተባረረ በኋላ ሲኒማ ቤቱንና ባሩን ደግሞ የያዘው የተባለ የግሪክና የኢትዮጵያ ክልስ እንደነበር የሲኒማው ማሳያ ሞተር በኢጅነርነት የሚሰሩ የነበሩት አቶ ተካቦ የነ ዮሀንስ እና ታፈረ አባት ነበሩ ድህረ ጣሊያንስ ጎንደር ምን ትመስል እንደነበር በስሱ እንቃኝ! ብዙ መረጃወች እንደሚያመለክቱት በ 1933 ዓ/ም ወይንም እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር በ1941 ዓ/ም ጦርነቱ ከተጠቃለለ በኋላ የወጣው የጠላት ጦር ከኢትዮጵያ ከወጣ በኋላ በድምሩ 130,000 (አንድ መቶ ሠላሳ ሺህ) ጣሊያኖች ኢትዮጵያ ውስጥ እንደነበሩ ብዙ የታሪክ መዛግብት ይጠቁማሉ። ከእነኚህ 130,000 ነጭ ጣሊያኖች ውስጥ 70,000 የጦር እስረኞችና 60000 ደግሞ ሲሺሊያን ነበሩ። የእንግሊዝ መንግስት ቀን ተሌት አፄ ኋይለ ሥላሴን ጣሊያኖች ከኢትዮጵያ አንድም ሳይቀሩ ሙልጭ ብለው እንዲወጡ ተፅእኖ ቢፈጥሩም በንጉሡ ዘንድ የእንግሊዞች ግፊትተቀባይነት አለገኘም። የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥትና በዙሪያቸው ወይንም በአካባቢያቸው በስልጣን እርከን ውስጥ የነበሩ መሳፍንቶችና አርበኞች ቢያንስ አንዳንዶቹ በተለይም የእጅ ሙያ ያላቸው ጣሊያኖች እንዲቆዩ ፍላጎታቸውን በግልፅ ማሳየት ጀመሩ። ከሁሉም በላይ የቴክኒሻኖች አስፈላጊነታቸው በጣም ሰፊ ስለነበር እነኝህ ጣሊያኖች የመጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን፣ የህንፃ ስራወች ጆሜትሪ፣ የመኪና ጥገና በሆስፒታሎች ለማገዝ እና ብዙ ሥራዎችን ለማከናወን ያገለግላሉ በሚል እምነት ነበር ብዙወቹ በፍላጎታቸው ኢትዮጵያ ውስጥ የቀሩት። በዚህ ምክንያት ጎንደር ውስጥም የተወሰኑ ጣሊያኖች ነበሩ። ሥራም ሳይንቁ ህዝቡን መስለውና ተመሳስለው ኑሮ ጀመሩ። ለምሳሌ ያህል ብልኮ ከቀድሞው ወወክማ ፊት ለፊት ከአቶ ደርበው ቡና ቤት ጎን ጎሚስታ ነበር ባለቤቱ ጣሊያናዊ እርጅና ሲጫጫነው አርበኞች አደባባይን እንድ ተጠለፈ አውሮፕላን በቅጠል ብጣሽ ቆርጦ እንደ ጭራ ይጠቀም ነበር። ወደመጨረሻው አካባቢ አቶ ሰጠኝ የተባሉ የጎንደር ተወላጅ እዚያው ይሰሩ የነበሩ በባለቤትነት የያዙት ይመስለናል። ሁላችሁም እንደምታውቁት ፒያሳወች ወደ ብልኮ መሄድ ስለሚከብደን:-) ሌላው ቢጋ የተሰኘ ጣሊያናዊ ሲትሮን የፈረንሳይ መኪና በመጠቀም ነበር ፍራፍሬና ወተት ለታላልቅ ሆቴሎችና ግሮሰሪ መደብሮች እንዲሁም ለባለ ፀጋ ጎንደሬወች ከአባሳሙዔል እርሻ በማጓጓዝ ያከፋፍል ነበር። ጣሊያን ልክ ሲወጣ በዚይን ዘመን አባባል ጎንደርን በአገረ ገዥነት ከደርግ በኋላ ደግሞ አስትዳዳሪ ነው የሚባለው አገረ ገዥ የነበሩት የንጉሡ ልጅ አልጋ ወራሽ እንደነበሩ ይነገራል። በዚህ ጊዜ ጎንደር ምንም ዓይነት የወታደር ባጀት ስላልነበረው አልጋ ወራሽ የጎንደር ነጋዴወች ለመንግስት ብድር እንዲያበድሩ ይጠይቁ ነበር። በዚያን ጊዜ ነበር በጊዜው የታወቁት አዲስ ዓለም የሚኖሩት የጎንደር ቱጃር መረቀኔ መሐመድ 30,000 ጠገራ ብር ወይንም ማርትሬዛ ለመንግስት ያበደሩት። መረቀኔ መሐመድ በዚህ አሳቢነታቸውና ሀገር ወዳድነታቸው በከተማው በነበሩ ጠጅ ቤቶች ማታ ማታ መረዋ ድምጥ ያላቸው የጎንደር ሊቀ መኳሶች እንዲህ እያሉ ይገጥሙ ነበር ….የሀበሻ ወታደር የሚበላው አጥቶ ….መርቀኔ መሐመድ አበላወ ሸምቶ እየተባለላቸው ላሳቢነታቸውና ለሀገር ወዳድነታቸው በግጥም ይወደሱና ይመሰገኑና ነበር። ለሀገር መስራት ሁሌም ያስመሰግናልና። አሁንም ፒያሳወች እዚያው ፒያሳ ላይ እናጠንጥንና የአሁኑ ቋራ ሆቴል ጣሊያን እንደወጣ አቶ ጌጡ ልዋጥህ ን አድሰው ግልጋሎት መስጠት ከጀመሩ በኋላ ይህ ሆቴል በጠላት የተገነባ ስለሆነ ወደ መንግስት ይዞታ መዛወር አለበት በማለት አገረ ገዡ በንጉሡ ልጅ አልጋ ወራሽ ትእዛዝ ተወስዶ ለወንድማቸው ለልዑል መኮንን ተሰጠ። ከዚያም ልዑል መኮንን ሲያርፉ ሆቴሉ ለረዥም ጊዜ ተዘግቶ ከኖረ በኋላ ፊታውራሪ ተስፋየ አስናቀ እና አቶ ኪዳኔ በሽርክነት አድሰው እንደገና ከፈቱት። ምንም እንኳ ጣሊያን ቤቱን ቢሰራውም ቦታው የመድሀኒ ዓለም ቤተክርስቲያን ለመሆኑ ብዙ መረጃወች አሉ። በክፍል አንድ ላይ ለመጠቆም እንደሞከርነው ጣሊያን ሲገባ የከተማዋ ነዋሪ ወደ ገጠር የሸሸው ሸሸ ሌላው ደግሞ በረሀ በመግባት ለነፃነቱ ይዋጋ ነበር። ለዚህም ነበር ከነፃነት በኋላ የመሬት ባለቤቶች የይገባኛል ክርክር የጀመሩት። ለምሳሌ ያህል ፒያሳ ሳንወጣ አሁን ያለው አይቀር ሆቴል ልክ ጣሊያን ሲወጣ ራስ ውብነህ ሆቴል ይባል ነበር። ባለቤቱም አርበኛው ራስ አሞራው ውብነህ ንጉሡ የሰጧቸው ነበር። ይህ በዲህ እንዳል የመሬቱ ባለቤት ግን እሙሀይ አጀቡሽ ጉበና የተባሉ የትንሽቱ አራዳ ነዋሪ ለ30 ዓመታት የርስት የይገባኛል ክስ ላይ እንደነበሩ ድፍን ጎንደር ያውቃል። እሙሀይ አጀቡሽ የደጃዝማች ካሣ መሸሻ አማት ነበሩ። ሲኒማ ቤቱን ያደሱትና ሥራ ላይ እንዲውል ያደረጉት፣ በጣም በስራቸው የተመሰገኑት የጎንደር አገረ ገዥ ጀኔራል መርዕድ መንገሻ ()ነበሩ። ግማሹ የሲኒማ ቤቱ አዳሬሽና ቡናቤቱ የተገነባበት መሬት የተወሰነው የወይዘሮ ድንቅነሽ የተባሉ መሀን ሴት እንደነበሩ ገሚሱ ደግሞ አራጣ በማበደር የሚታወቁት የወይዘሮ ነጠረች ዕርስት እንደነበረና በኋላም ወይዘሮ ነጠረች ክርክሩን በማሸነፍ ከሲኒማቤቱ ጀርባ ኤክስፖ ሆቴል ብለው እንደገንቡ ይታወቃል። የአፄ ፋሲል ቤተ መንግስት () ስለመበላሸትና ራስ አሥራተ ካሣ የጎንደር አገረ ገዥ የገጠማቸውን ችግር ተለምዶዋዊውና ፍቅራዊው ሰላምታችን ይኸን የሽቦ ገመድ አልባ ዘመናዊ መገናኛ አሳብሮና ሰንጥቆ በያላችጉሁበት ይድረስልን እንላለን። ….በሉ እንግዲህ ወደ ፒያሳ እንውጣ ሱቁን ከተማውን አስሰን እንድንመጣ ወደ ቀደመው ጉዳያችን እንመለስንና ክፍል ሁለትን የደመደምነው የፋሲል በተመንግስት የገጠመውን ችግር እናነሳለን ብለን ነበር የተለያየነው ይሁንና አንዱን እንደ ስሚዛ ስንመዝ ሌላው ተከተለና አሁንም ስለ ጎንደርና ጣሊያን ሰለሰሯቸው ህንፃወች ሌሎች አዳዲስ የታሪካዊ መረጃወች እናንተም የምትካፈሉበት ይዘን እዚያው ፒያሳ ጀምረን ወደ ጨዋ ሰፈር ካልመሸብን ብልኮ ደርሰን ወደ ኦቶባርኮ እንዋባለን። የወራሪው የጣሊያን ፋሽስት መንግስት ጎንደርን ለምን መርጦ ከተመ የሚል ጥያቄ በኛም በእናንተም አዕምሮ አጭሯል ብለን እናምናለን። ብዙ መላምቶች ይኖሩ ይሆናል እኛ ያገኘነውን መረጃ እናቅምሳችሁ። በኢትዮጵያ የቀደምት የነገስታት ታሪክ ማለትም ሰለሞናዊ ነገስታት ተብለው የሚጠሩት ሁላችንም እንደምናውቀው ከየኩኑ አምላክ እስከ አፄ ሱሲኒወስ ድረስ ቋሚ ነገስታቶች የቆረቆሩት ከተማ አልነበረም። በዘመናቸው የነገሡ ነገስታት አንዱ በጀመረው ከተማ የመቀጠልና የማስፋት ዝንባሌ አልነበረም ዳሩግን ዘላናዊ ንግስና እንደነበራቸው ነው የሚተረከው። አፄ ፋሲለደስ (ፋሲል) አባታቸው አፄ ሱሲኒወስ የቆረቆሯትን ደንቀዝንና ቤተምንግስቱን ትተው ወደ ጎንደር እስኪመጡ ድረስ ማለትም በ1628 ዓመተ ምህረት በፈረንጆች 1636 ማለት ነው ጎንደር በጣም ትንሽ መንደርና ብዙ የሕዝብ ቁጥር አልነበራትም። ይህን እውነታ አፄ ፋሲል አስረግጠው በማወቅና በመረዳት ከዚያም በተጨማሪ ጎንደር ዙሪያዋን በተራሮች ሰንሰለት የተከበበች ስለሆነች ከጠላት ለመመከት የሚስችል ቁልፍ ቦታ ናት ብለው እራሳቸውን በማሳመናቸው ሌላውና ዋና የወፋሲሳኔቸው ምንጭ ደግሞ ጎንደር ሁለት ታላላቅ ወንዞችን ማለትም አንገረብንና ቀኋን የተንተራሰች በመሆኗ ከሌሎች ቦታወች ሁሉ አንቺ የተባረክሽ ነሽ እና ንግስናየ ቤተ መንግስቴ እና ግዛቴን እስከ ዐለተ ሞቴ እዝችው ከአንቺ ጋር ይሁን በማለት አፄ ፋሲል የአባታቸው አፄ ሱሲኒወስን ቤተምንግስት ትተው ከደንቀዝ ሰሜናዊ ምዕራብ ወደ ምትገኘው ወደ ጎንደር ሰራዊታቸውን አስከትለው በመጓዝ ግዛታቸውን ያዛወሩት። ጎንደር እንደገቡም ቤተ መንግስታቸው እስኪታነፅ በቀጥታ ያረፉት ከታሪካዊው ጃንተከል ዋርካ ሥር አጅባራቸውን ተክለው እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ። በዚህ ጊዜም ነበር አውሮፓዊያን ወደ ጎንደር መምጣት የጀመሩት። ብዙ የታሪክ ተመራማሪወች እንደፃፉት መፃህፍት እንደፃፉት በታሪክም እንደምንሰማው ፒተር ሄይሊል የተሰኘ ጀርመናዊ ህግና ሥነ-ሃይማኖትን በፈረንሳይ ዋና መዲና በፓሪስ (ከ 1620 እስከ 1624) በመማር ትምህርቱን በማጠናቀቅ በርካታ ተመራማሪ ተማሪዎች ጋር በመሆን መጀመሪያ ወደ ግብፅ ቆይታ በማድረግላ እ.ኤ.አ በ 1629 ወደ ኢትዮጵያ በመጓዝ በሀገሪቱ ውስጥ ተፅዕኖ ፈጣሪ አገልጋይ, አስተማሪ እና ሐኪም በመሆን ንጉስ ፋሲለደስን አግልግሏል። በዚያን ጊዜ የነበሩ የቤተክህነት አባቶችንንና ቀሳውስትንም የግሪክና የይብራይስጥ ቋንቋን በማስተማር ይረዳ እንደነብር ታሪክ ያውሳል። አፄ ፋሲልም በሚሰራቸው ስራወች በጣም በመደሰት ማሪያማዊት የተሰኘች ሴት ልጃቸውን ለፒተር ለመዳር ውጥን ላይ እንደነበሩ የአዲስ ኪዳን መፅሐፍ ቅዱስን ወደ አማርኛ እዛብቶ ሲትርጉም ስላገኙት በአስቸኳይ ከሀገር እንዲወጣ ንጉስ ፋሲል በማዘዛቸው ከሀገር ተባረረ። ከላይ ለማሳየት እንደሞከርነው አፄ ፋሲል ጎንደርን ለከተማነት ያጩበት ሁለት ውሳኒያዊ ነጥቦች ነበሩ። የፋሽስት ጣሊያን የጦር ኋይል ኢትዮጵያን ከወረረ በኋላ ጎንደር ከተማ ላይ ያተኮረበት ዋናው ምክንያቱ ሁለቱ ወንዞች ማለትም የአንገረብና የቀኋ እንደነበሩና ሌላው ደግሞ የጎንደር አካባቢው የሰባ መሬትን በመስኖ እየታገዘ መለስተኛ እርሻወችን ለመመስረት እቅድ እንደነበራቸው እኛ ፒያሳወች ቆፍረንና ፈልሰን ያገኘናቸው ታሪካዊ መረጃወች አረጋግጠውለናል። በቅምሻ ቁጥር አንድ ጣሊያን ጎንደር ከተማ 352 ህንፃወችን መገንባቱን እናስታውሳለን። እነኝህ በመቶ የሚቆጠሩ ህንፃወች ከመገንባታቸው በፊት የከተማዋን ፕላን ያወጣው ገራርዶ በዕሲዮ (ፎቶውን የመልከቱ) የተሰኘ ኢንጂነር ነበር። በ1918 ዓመተ ምህረት ወይንም በፈረንጆች በ1926 በሮማን ኢንጂነሪንግ በዲግሪ የተመረቀ ሲሆን ከዚያም በ1923 ዓመተ ምህረት ወይንም በፈረንጆች በ1931 በፍሎራንስ ዩኒቨርሲቲ የህንፃ ትምህርት ቤት ተመርቆ ኢትዮጵያ ጎንደርና ደሴን ከዚያም ደግሞ የአልባኒያን ዋና ከተማ ቲሪና ማስተር ፕላን በ1939 በፈረንጅ ምስራቱን ታሪክ ያስተምረናል። ገራርዶ የጎንደርን ማስተር ፕላን ሲሰራ የተሰጠው ትዕዛዝ የሚሰሩ ቤቶች ሁሉ አንገረብንና ጣና ሀይቅን እንዲያሳዪ ሆነው እንዲገነቡ ነበር የተሰጠው የስራ ሀላፊነት። በዚህም ምክንያት ጎንደር ጨዋ ሰፈር 2020 ጫማ ከባህር ወለል በላይ በመሆኗና አንገርብ ወንዝን በደንብ ስለምታሳይ ታቅዶ በጠቅላላው 35 ህንፃወች ሲገነቡ ከነዚህም ውስጥ ሰባት ቪላዎች እና 28 ህንጻዎች ተገንብተዋል። ሌላው ጨዋ ሰፈር ውስጥ ሁለት ባንኮችን ባንካ ዲ-ኢታሊያና እና ባንኮ ዲ-ሮማ . አንደኛው አሁንም በባንክነት እያገለገለ የሚገኘው ዋና ባንክ በመባል የሚታወቀው ሲሆን ሁለተኛው በአሁኑ ሰዓት ከግልጋሎት ውጭ ሲሆን ለረጅም ጊዜ በእስር ቤትነት 1ኛ ፖሊስ ጣቢያ የነበረው ነው። ጨዋ ሰፈር ይኖሩ የነበሩ ጣሊያኖች በእረፍት ጊዚያቸውን የሚያሳልፉት አንገረብ በመዋኘት እንደነበርም ይነገራል ለዚያም ነበር አንገረብ ጥሊያን መዋኛ በመባል ይጠራ የነበረው። አሊቤርጎ ቻው ወይንም (እቴጌ መነን///ተራራ ሆቴል) እዚህ ፕላኑ ላይ እንደሚታየው መዋኛ፣ ቡና ቤት፣ የመሬት ቴንስ እንዱም ብዛት ያላቸው መኝታ ቤቶችን ያካተተ ትልቅ ሆቴል ሲሆን የታለመለት ለፋሲል ቤተ መንግስት እንዲቀርብና አንገረብንና ጣናን እንዲያሳይ ሆኖ ነበር የተገነባው። የታሪክ መረጃወቻችን እንደገለፁት በግንባታው ረዥም ጎዜ ወስዶ ነበር። አሊቤርጎ ቻው ግንባታ በነበረበት ወቅት ሁለቱ ትናንሽ ሊቶሮዮ እና ቺንጎ የተሰኙ ሆቴሎች እያንዳንዳቸው 7 የመኝታ ክፍሎች የነበሯቸው እንደነበሩ ታሪክ ያወሳል። ሁለት ምግብ ቤቶች ና የተባሉ ጣሊያኖችን ግልጋሎት ይሰጡ ነበር። ቸር ይግጠመን የኢትዮጵያ ከተሞች
13930
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8A%AE%20%E1%8D%96%E1%88%8E
ማርኮ ፖሎ
ማርኮ ፖሎ (1254 - ጥር 8፣ 1324) ጥንታዊው የጣሊያን ተጓዥ እና ነጋዴ ነበር። ታዋቂነትም ያተረፈው በተለይ ወደቻይና እና ሞንጎሊያ ከተጓዙት አውሮጳውያን ቀደምትነት ስለነበረው ነው። በዚህ ምክንያት ከሱ በኋላ ዘግይተው የተነሱት እነ ክርስቶፎር ኮሎምበስ ሳይቀር ለሱ ከፍተኛ ግምት እና አድንቆት እንደነበራቸው ታሪክ ይዘክራል። ት 1 17 አመት ሲሞላው ከጣሊያን ቬኒስ ከተማ በመነሳት፣ መጀመሪያ በጀልባ ከዚያም በእግሩና በግመል ተራሮችን በርሃን አቆራርጦ ቤይቺንግ ቻይና (በድሮ ስሟ ካቴ]) ለመድረስ ችሏል። በጊዜው ቻይና ትመራ የነበረው በሞንጎሉ መሪ ኩብላ ካህን የሚባለው የጌንጊዝ ካህን ልጅ ነበር። ስርዓቱም የዩዋን ሥርወ መንግስት ይባል ነበር። ለሚቀጥሉት 17 ዓመታት በኩብላ ካህን ቤተመንግስት አስተዳደር ተሰጥቶት መንግስቱን አገልግሏል። ከዚያም ወደ ጣሊያን በውቅያኖሶች አቋርጦ ተመልሷል። ወደ600 የሚሆኑ አብሮ ተጓዦች ግን በበሽታና በጥቃት ሞተዋል። ይህ ተጎዥ ኑድል የተባለውን የቻይኖች የምግብ አይነት ወደ አገሩ ጣልያን በማምጣት የፓስታ ስራ አሰራርን ለጣሊያኖች ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋውቋል። በጣሊያኖች እርስ በርስ ጦርነት ተማርኮ እስር ቤት ከገባ በኋላ ለእስር ጓደኛው ርስቲቸሎ የነገረውን ታሪክ ረስቲቸሎ ጽፎ በማሳተም ለማርኮ ፖሎ በአውሮጳ ዙርያ ታላቅ መታወቅን አስገኝቶለታል። ማርኮ ፖሎ በነበረበት ዘመን ስለኢትዮጵያ የመዘገበው «አበሻ በሌላ አጠራር መካከለኛው ህንድ ወይም ሁለተኛው ህንድ ተብሎ ይታወቃል። ዋናው ልዑሉ ክርስቲያን ሲሆን በሱ ስር 6 ሌላ ንጉሶች አሉ። ሶስቱ ክርስቲያን ሲሆኑ ሶስቱ ደግሞ እስላም ናቸው። ሁሉም ግን በክርስቲያኑ ንጉስ ስር ይተዳደራሉ። ንጉሰ ነገስቱ በአገሪቱ መካከለኛ ስፍራ ይኖራል [ምናልባትም ተጉለት? ]። የእስላሙ ዋና ንጉስ የሚኖረው ኤደን አካብቢ ነው። የአቢሲኒያ ሰወች በጣም ጠንካራ ናቸው፣ ታላቅም ጦረኞች ናቸው፣ ከአዳል ሱልጣኔት፣ ከኑቢያ መንግስት እና ሌሎች መንግስታት ጋርም የማያቋርጥ ውጊያ ያደርጋሉ። በዚህ ምክንያት በህንድ ውስጥ ካሉ ወታደሮች ሁሉ ዋና ሃይለኞቹ እነሱ ናቸው። እንደሰማሁት፣ በ1288 የሃበሻው ንጉስ ወደ እየሩሳሌም በመሄድ የኢየሱስ ክርስቶስን መቃብር ለመሳለም ፈልጎ የሱ መኮንኖች ይህ የሚያስከትለውን ችግር በተለይ የእስልምና ተከታይ መንግስታት በአካባቢ መብዛትን ግምት ውስጥ በማስገባት በሱ ምትክ በሃይማኖተኛነቱ ይደነቅ የነበረ ጳጳስ እንዲሄድ አድርጎ ይህ ጳጳስ እየሩሳሌም በመሄድ ስለት አስገብቷል። ጳጳሱ ሲመለስ ግን አዳል ውስጥ ተማርኮ የአዳሉ መሪ ጳጳሱ እስልምና እንዲቀበል ቢመክረው እምቢ በማለቱ ጳጳሱ እንዲገረዝ [እንዲሰለብ?] አደረገ። ከዚያም ጳጳሱ ወደ አገሩ ከተመለሰ በኋላ የተደረገበትን ግፍ ለንጉሱ ነገረው። ንጉሱም ወዲያው ፈረሱን አስጭኖ ከሰራዊቱ ጋር አዳልን ለማጥፋት ዘመተ። የአዳሉም ልዑል የአቢሲኒያ ጦር እንደዘመተበት በሰማ ጊዜ ሁለት ባለ ብዙ ሰራዊት እስልምና ተከታይ ንጉሶች ከእንዲረዱት ጥሪ አደረገ። ነገር ግን የሃበሻው ንጉስ ስላሸነፋቸው የኤደንን [አዳል?] ዋና ከተማ [ዘይላ?] በመቆጣጠር ከተማይቱን በዘበዘ። ይህም ለጳጳሱ የተደረገበትን ጉዳት ለመበቀል ነበር። የአቢሲኒያ ሰወች የሚበሉት ስንዴ፣ ሩዝ፣ እና ወተት ነው። የምግብ ዘይት የሚሰሩት ከሰሊጥ ሲሆን የተትረፈረፈ ሰብልን ያመርታሉ። ዝሆኖች፣ አንበሶች፣ ቀጭኔወች፣ እንዲሁም ፍየሎችና የተያዩ የወፍ ዝርያወች በአገራቸው ይገኛሉ። ሰውን የሚመስሉ ዝንጀሮወችና ጦጣወች እንዲሁም ብዙ የተለያዩ እንስሳቶች አሉ። ውስጠኛው የአገሪቱ ክፍል ብዙ ወርቅ አለው፣ ነጋዴወችም በራሳቸው ፈቃድ በአገሪቱ ውስጥ ይንቀሳቀሳሉ ምክንያቱም ብዙ ጥቅም ስለሚያገኙበት።» ማርኮ ፖሎ ይህን ጽሁፍ የጻፈው በ1290 እ.ኤ.አ. ሲሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ከተገኙ ገድላት ጋር አንድ አይነት ታሪክ እንደሆነ ሳልት የተባለው የእንግሊዝ ተጓዥ አረጋግጧል። የማርኮ ፖሎ ጽሁፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተገኙ ገድላት ጋር ተመሳሳይ ታሪክ ያስቀምጥ እንጂ የንጉሱን ስም ግን አልጻፈም። የማርኮ ፖሎን ጽሁፍ ያጠኑ ታሪክ ተመራማሪወች፡ ለምሳሌ ትሪንግሃም እና ሪቻርድ ፓንክረስት ንጉሱ አጼ ይግባ ጽዮን እንደነበር ለማረጋገጥ ችለዋል። የኢትዮጵያ ታሪክ ታሪካዊ ተጓዦች የጣልያን ሰዎች
14146
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%99%E1%88%B4%20%E1%89%80%E1%88%B5%E1%89%B0%E1%8A%9B
ሙሴ ቀስተኛ
ሙሴ ቀስተኛ (ሴባስቲያኖ ካስታኛ)ጣልያንኛ፡ ) ይሄ ሰው በአድዋ ጦርነት የጣልያን መንግሥት አገራችንን ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛትነት ለመግዛት ከገቡት ወታደሮች አንዱ ሲሆን፣ ለወረራ የመጣው የጠላት ኃይል በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ እና በሠራዊታቸው ቆራጥነት አድዋ ላይ ድል ሲሆን ተማርኮ የቀረና እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ ኢትዮጵያ ውስጥ የኖር ኢጣልያዊ ነው። ሙሴ ቀስተኛ በ፲፰፻፷ ዓ/ም በሲሲሊ ደሴት አይዶኔ በሚባል ሥፍራ ተወለደ። ስለልጅነት ዘመኖቹ እና በወጣትነቱም የጣልያንን የጦር ሠራዊት እንዴት እና ለምን እንደተቆራኘ መቼ፣ ከማን ሠራዊት ጋር፣ የትኛው ወደብ ላይ ኢትዮጵያ ላይ ለመዝመት እንደመጣ በእርግጠኛነት ባይታወቅም፤ ድሉ የኢትዮጵያ ሆኖ ሙሴ ቀስተኛ በምርኮኛነት በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሠራዊት እጅ ወደቀ። ከተማረከም በኋላ በፈቃዳቸው እዚያው ኢትዮጵያ ውስጥ ከቀሩት ብዙ ጣልያኖች አንዱ እንደነበረና በተግባረ ዕድ ሞያው ታዋቂነትን አትርፎ በምህንድስና ተግባራት እንደተሰማራና ኢትዮጵያም ውስጥ እስከ ሁለተኛው የፋሽስት ኢጣልያ ወረራ ድረስ ኖሯል። በወረራውም ጊዜ የጣልያንን ጦር ዓለቆች በሰላይነት እንዳገለገላቸውና በመጨረሻም በአንድ ቆራጥ ኢትዮጵያዊ አርበኛ እጅ ሕይወቱን እንዳጣ ስለእሱ ከተጻፉ ጥቂት ታሪካዊ መሥመሮች ላይ እንገነዘባለን። ይሄ ሰው በአገራችን የታሪክ ዘገባዎች ላይ፣ ምናልባትም በታሪካችን ላይ በተጫወተው ሚና ረገድ በቂም ባይሆንም፣ ‘ብቅ፣ ጥልቅ’ እያለ ሲመዘገብ እናገኘዋለን። ስለዚህ ሰው አሟሟት ፀሐፊው በልጅነት ዘመን ያጠናው በመሆኑ ስለሰውዬው ማንነት እና አመጣጥ ለመመርመር ላደረገው ጥረት መነሻ ነው። ከአድዋ ድል መልስ ፔጎሎቲ የሚባል ጸሐፊ “ኢጣልያዊው በንጉሥ ምኒልክ ቤተ መንግሥት” በተሰኘው መጽሐፉ ላይ ሙሴ ቀስተኛ በፋሽሽት ኢጣልያ ሁለተኛ የሙከራ ጊዜ ፣ በአድዋ ጦርነት ላይ የተሳተፈ አዛውንት እንደነበረና አዲስ አበባ ላይ በተግባረ ዕድ ችሎታው በዳግማዊ ምኒልክ እንዲሁም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተወዳጅነትን እንዳፈራ ይዘግብና ለጥቆም በ ‘ሕዝብ ሥራ ሚኒስቴር’ ውስጥ ዲሬክቶር ሆኖ ይሠራ እንደነበር፣ በተለይም የራስ ደስታ ዳምጠውን አክስት ካገባ በኋላ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ምን ያህል አክብሮት እንዳገኘ ይነግረናል። በትውልድ አገሩ አይዶኔ ደግሞ ስለእሱ የታተመ ጽሑፍ ላይ አንጀላ ሪታ ፓሌርሞ ከዚሁ ከወይዘሮ በላይነሽ ጋብቻ ማሪያ እና ጁሴፒና የተባሉ ሁለት ሴት ልጆች እንደተወለዱለት ታበሥራለች። ‘የባሕላዊ ቅርስ ሽግግር’ በካዛንችስ፣ አዲስ አበባ የታሪካዊ ቤት አርዕያዊ ጥገና’ (እንግሊዝኛ “ 2005) በሚል ዕትም ላይ በሠፊው፤- በአድዋ ጦርነት ተማርከው ወደ አዲስ አበባ የመጡት የጣልያን ወጥቶ አደሮች አብዛኞቹ በግንባታ እና የመንገድ ሥራ መስክ ተሰማርተው እንደነበር ይገልጽና ሙሴ ቀስተኛም ከነዚህ አንዱ እንደነበር ያረጋግጥልናል። ይኼው ዕትም ሙሴ ቀስተኛ የካቲት ፳፫ ቀን ፲፱፻፬ የተመረቀውን የገነተ ጽጌ መናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ዕቅድ የነደፈው መሐንዲስ እንደነበረ እና በ፲፱፻፴ ዓ/ም የታተመው “በምሥራቅ አፍሪቃ የጣልያን ግዛት” መምሪያ (ጣልያንኛ፣ , 1938) ሕንጻውን በማሞገስ እንደተነተነው አስቀምጦታል። ሆኖም የቤተ ክርስቲያኑን ዕቅድ የነደፈው መሐንዲስ የግሪክ ተወላጁ እንደነበረና ሙሴ ቀስተኛ የቤተ ክርስቲያኑን ግንባታ ተኮናትሮ የሠራ እንደሆነ ሌሎች ታሪካዊ ዘገባዎች ይገልጻሉ። ቀስተኛ ከዚህም ሕንጻ ሌላ በ፲፱፻፪ ዓ/ም የተመረቀውን ዘመናዊ የ'አቢሲኒያ ባንክ' ሕንጻ ኢጣልያዊው መሐንዲስ ቫውዴቶ () ባዘጋጀው ንድፍ መሠረት ሙሴ ቀስተኛ እንደሠራው ሪቻርድ ፓንክኸርስት ዘግቦታል። የፋሽሽት ወረራ ዘመን በጥቅምት ወር ፲፱፻፳፰ ዓ/ም ወረራው ሲጀመር የኢትዮጵያ ወጥቶ አደሮች እና አርበኞች የጠላትን ጦር ለመከላከል በሰሜን፤ በደቡብ፤ በምሥራቅ እና በምዕራብ ግንባሮች ተሠማርተው የተቻላቸውን ያህል ተቋቋሙ። ሆኖም የፋሽሽት ሠራዊት በዘመናዊ መሣሪያ እና የመርዝ ቦንብ አይሎባቸው በግንባር ለግንባር ግጥሚያ ይሸነፉና ንጉሠ ነገሥቱም በግንቦት ወር ተሰደው ወደ እንግሊዝ አገር ሄዱ። አገሪቷም በጣልያን ቁጥጥር ስር አደረች። የግራዚያኒ ሠራዊት ግን በደቡብ ግንባር ራስ ደስታ ዳምጠው እና ደጃዝማች በየነ መርዕድ ፤ በምዕራብ የባላምባራስ ገረሱ ዱኪ አርበኞች በሰሜን ሸዋ ደግሞ የራስ አበበ አረጋይ ሠራዊት አልበገር ብለው አስቸግረውት ቆዩ። ግራዚያኒ በድርድር እነኚህን መሪዎች ለማስገባት ባደረገው ጥረት መልእክተኛና ሰላይ አድርጎ የመረጠው የኢትዮጵያውያንን ባህል ለ አርባ ዓመታት ያጠናውንንና የራስ ደስታን አክስት ያገባውን ይሄንኑ ሙሴ ቀስተኛን ነበር። በዚህ ዓላማ መጀመሪያ የተላከውም ወደ ራስ ደስታ ዳምጠው ሲሆን፣ ታኅሣሥ ፲፱ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በባሌ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ ቡላንቾ (አርበጎና) የሚባል ሥፍራ ላይ ሁለቱ ተገናኝተው ለሁለት ሰዓት ያህል ተወያዩ። ቀስተኛ ከዚህ ድርድር በኋላ እንደገመተው፣ ራስ ደስታ እጃቸውን እንደሚሰጡና የጭፍሮቻቸውን፣ በተለይም የጣልያንን ወገን ከድተው ከሳቸው ጦር ጋር የተቀላቀሉትን ኤርትራውያን እስከሚያሳምኑ ድረስ ጊዜ ያስፈልጋቸዋል በሚል ግምገማ ነው። ራስ ደስታ የካቲት ፲፭ ቀን ቡታጅራ አካባቢ ላይ በትግራይ ተውላጅ ደጃዝማች ተክሉ መሸሻ ተይዘው በጠላት እጅ ወዲያው ተረሽነው ሞቱ። የሙሴ ቀስተኛ ስም በታሪካችን ዘገባ ላይ እንደገና ብቅ የሚለው በ ግንቦት ወር ፲፱፻፴ ዓ/ም ላይ ሲሆን አሁንም እንደቀድሞው የግራዚያኒ መልእክተኛና ሰላይ በመሆን ለዕርቅ ስምምነት ከ ራስ አበበ አረጋይ ጋር ግንደበረት ላይ ተገናኝቶ ለግራዚያኒ አርበኞቹ ለመስማማት የሚፈልጉ መሆናቸውን አስታወቀ። የሠራዊቱንም ብዛት በተመለከተ የስለላ ዘገባውን ለግራዚያኒ አስታውቆ በተከተለው የፋሽሽት ጥቃት ብዙ ኢትዮጵያውያን አርበኞት አልቀዋል። ሦስተኛውና የመጨረሻው ተልዕኮው በ ጥቅምት ወር ፲፱፻፴፩ ዓ/ም ሲሆን በዳቄሮ በሚባል ሥፍራ ላይ ወደነበሩት ባላምባራስ (በኋላ ደጃዝማች) ገረሱ ዱኪ ነበር። እዚህ ሥፍራ ላይ ከሦስት ባላባቶች ጋራ የመጣው ቀስተኛ የሰባ አንድ ዓመት ሽማግሌ፣ ነጭ ጸጉር እና ባለሙሉ ጺማም ሲሆን አርበኞቹን ሰብስቦ በተጣራ አማርኛ ‘ንጉሠ ነገሥታችሁ እንኳን ትቷት የሄደውን አገር እናንተ በዚህ በልጅነት እድሜያችሁ ቅማል ወሯችሁ የማይቀርላችሁን ሞት ገደል ለገደል ከምታባርሩ ይልቅ ገብታችሁ ከኢጣልያ ጋር አገራችሁን በልማት ብታገለግሉ አይሻልም ወይ? መሣሪያችሁን አስረክባችሁ የገባችሁ እንደሆነ ኢጣልያ ትምራችኋለች፤ ሹመት እና ሽልማትም ትሰጣችኋለች” ብሎ ሲሰብካቸው ወጣት አርበኞቹም ቀደም ሲል በ፲፱፻፴ ዓ.ም ይኼው ሰላይ ወደ ራስ አበበ አረጋይ ዘንድ ሄዶ የጦሩን ኃይል ከሰለለ በኋላ ብዙ አርበኛ እንዳስፈጀ ሰምተው ስለነበር እነሱንም እንደዚሁ ለማስፈጀት እንደመጣ ተገንዝበውታል። ከሰበካው በኋላ ወደ እኩለ ቀን ሲሆን ተበተኑ። ከዚህ በኋላ ሙሴ ቀስተኛ ወደሠፈረት ቦታ፣ በመጣባት በቅሎ በባሻ ኪዳኔ ወልደመድኅንታጅቦ ሲሄዱ፣ ባሻ ኪዳኔ ቀስተኛ የለበሰው ካፖርት በደም እንዳይበላሽ በማሰብ “ሐሩር ፀሐይ ነውና እንዳይውብቅዎት ካፖርትዎን ያውልቁት” ሲሉት “ልጄ ልትገለኝ ነው” አላቸው። ይሄኔ ባሻ ኪዳኔ ወልደ መድኅን በመውዜር ጠመንጃ ሲመቱት 'ማማ ሚያ፤ ኢጣልያ ለዘለዓለም ትኑር ለኢጣሊያ ስል ሞትኩላት' ብሎ ሲፎክር በሽጉጥ ራሱን መትተው ገደሉት። የለበሰውንም ሙሉ ገበርዲን ልብስና ካፖርት እንዲሁም የንግሥተ ነገሥት ዘውዲቱ ምስል ያለበትን የብር ሰዐትና በቅሎውን ከነኮርቻው ማረኩት። እሱም እንደተገደለ አብረውት መጥተው የነበሩት ባላባቶች ለጄነራል ናዚ አስታውቀው ኖሮ ሃያ ዓምስት ባታሊዮን ወታደርና ሃያ ስምንት አውሮፕላን ወደበዳቄሮ ዘምቶ ተርታውን ለሦሥት ቀን ሲከላከሉ ከቆዩ በኋላ አርበኞቹ ተሸንፈው ጠላትም የሙሴ ቀስተኛን እሬሳ አንስቶ ወሰደ። አርበኞቹም ከዚያ ሥፍራ ሸሽተው ሶዶ ላይ እንደገና ለስምንት ቀን ተዋጉ። አንቶኒ ሞክለር (እንግሊዝኛ፤ ) ስለቀስተኛ ሞት ሲያወሳን በስህተት በገረሱ ዱኪ ተሰቅሎ ሞተ ይለናል። ሆኖም የጣልያን መንግሥት ገረሱን ለሚገድልለት ሰው ፶ ሺህ ሊራ እንደሚሰጥ ማወጁንና በኋላ የጣልያን መንግሥት እንደራሴ፣ ዱካ ዳኦስታም ይሄንን ሽልማት እጥፍ እንዳደረገው ይነግረናል። ሙሴ ቀስተኛ በዚያው በ፲፱፻፴ ዓ/ም ከሞት በኋላ የጣልያን መንግሥትን የወርቅ የጦር ጀብዱ ሜዳይ (ጣልያንኛ፤ ) ተሸልሟል። የመዳልያውን አሰጣጥ የሚተነትነው ጽሑፍ በፋሽሽት ፕሮፓጋንዳ እና ሐሰት የተመረዘ ሲሆን ሙሴ ቀስተኛ በኢጣልያ መንግሥት ሥር የትውልድ አገሩን ሲያገለግል እንደሞተ ይነግረንና፣ “አንድ ፈሪ፣ አረመኔ የሽፍታ ዓለቃ (ገረሱ ዱኪን ማለቱ ነው!) ለውይይት ና ብሎ ጽፎለት በማታለል እጁን ሊይዘው መሆኑን ሲገነዘብ፣ እሱ ግን በዕድሜው የገፋ ቢሆንም እጁን ላለመስጠት ሲያመልጥ ተገደለ።” ይለናል። ሙሴ ቀስተኛ የኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ከ አድዋ ጀምሮ እስከ ፋሽሽት ወረራ ድረስ ለአርባ ዓመታት ትልቅ ሚና የተጫወተ፣ እንደውም ታሪኳም የነበረ ሰው ቢሆንም በትውልድ አገሩ ኢጣልያም ቢሆን በሚስቱና የልጆቹ አገር ኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ‘ብቅ፣ ጥልቅ’ ከማለት በስተቀር እምብዛም ስለሱ የተጻፈ ነገር የለም። ከአድዋ ጦርነት በኋላ በምርኮኝነት ኢትዮጵያ ላይ ይቅር እንጂ ከዚያ በኋላ ኑሮውን እዚያው ያደረገው በውዴታ ይሁን በግዴታ አይታወቅም። እጃንሆይ ምኒልክስ ዘንድ በማን አስተዋዋቂነት/አቅራቢነት ኖሯል የአራዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ዕቅድ ለመንደፍ የበቃው? በሕዝብ የሥራ ሚኒስቴር ውስጥ ዲሬክቶር በነበረበት ጊዜ ሌላ በሙያው የሠራቸው ነገሮች ምንድን ናቸው? ከራስ ደስታ ዳምጠው አክስት ጋር ለጋብቻ የበቃውስ በምን ሁኔታ ነበር? እነኚህንና የመሳሰሉ ብዙ ጥያቄዎችን ያስነሳል። ኢትዮጵያዊው ምሁር መርሳዔ ኀዘን ወ/ቂርቆስ (18 91 -1971 እ.ኢ.አ.) “ትዝታዪ ስለ ራሴ የማስታውሰው“ በሚለው የህይወት ታሪክ መፅሀፋቸው፤ ሙሴ ቀስተኛ ከሌላ ጣሊያናዊ ቴንቲኒ ባንዲ ከተባለ ጋር በንጉስ ዳግማዎ ሚኒሊክ ዕቅድ ከአዲስ አበባ እስከ አዲስ ዐለም ያለውን መንገድ በድንጋይ ንጣፍ ለማልበስ የቅድመ ምርመራ “ “ስራውን እንደሰሩ ማወቃቸውን ተርከዋል፤ በሌላ መፅሀፍ የወቅቷን አዲስ አበባ በፎቶግራፍ በሚያሳይ መፅሀፍ ኢጣሊያዊው መሀንዲስ ቀስተኛ ወደ እንጦጦ ማርያም ቤተ/ክርስቲያን የሚያመራውን የመንገድ ስራ በበላይነት ቀጥጥር ላይ እንደተሳተፍ ተገልፆል፤ ከሌላም ምንጭ እንደተገለፀውም በዐባይ ወንዝ ላይ ለተሰራው ድልድይም አቅጣጫዎችን መርቷል፡፡ ዋቢ ምንጮች አዲስ ዘመን ጋዜጣ ፣ ፴፰ኛ ዓመት ቁጥር ፴፰፣ ቅዳሜ ጥቅምት ፲፮ ቀን ፲፱፻፸፪ ዓ/ ም የኢትዮጵያ ታሪክ የጣልያን ሰዎች
11832
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%AD%E1%8C%80%E1%8A%95%E1%89%B2%E1%8A%93
አርጀንቲና
አርጀንቲና ወይም በይፋ አርጀንቲናዊ ሬፑብሊክ (እስፓንኛ፦ /ሬፑብሊካ አርሔንቲና/) በደቡብ አሜሪካ የሚገኝ አገር ነው። ዋና ከተማ ብዌኖስ አይሬስ ነው። መደበኛው ቋንቋ እስፓንኛ ሲሆን ቀበሌኛው በእስፓንያ ከሚሰማው ትንሽ ይለያል። ሌሎችም ቋንቋዎች የሚናግሩ ሕዝቦች አሉ፣ ወይም ኗሪ ቋንቋዎች እንደ ቀቿ፣ ወይም አውሮፓዊ ቋንቋዎች (በተለይ ጣልኛ፣ ጀርመንኛ) አርጀንቲና እ.ኤ.አ. ከ 1994 ጀምሮ በብሔራዊ መስተዳድር እና 24 ራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳድሩ መንግስታት የተዋሃደ የፌዴራል መንግስት ነው የተደራጀችው ቅድመ-ኮሎምቢያ ታሪክ የአርጀንቲና ቅድመ-ኮሎምቢያ ታሪክ በስፔን ወረራ እና ቅኝ ግዛት ከመደረጉ በፊት የአርጀንቲና ሪ ብሊክ የአሁኑን የአካባቢ ባህላዊ እድገት ያመለክታል ፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአርጀንቲና የሚቆጣጠሩት የመጀመሪያ የህዝብ ብዛት በሎስ ቶልዶስ እና በፒድራ ሞሱ ግኝት መሠረት በ 12 ኛው ወይም በ 13 ኛው ሺህ ዓመት ነው ፡፡ ፓፓታኒያ ፣ ፓምፓ እና ቾኮ አርሶ አደሮች በሰሜን ምዕራብ ፣ በኩዮ ፣ በሴራስራስ ደ ኮርዶባ እና በኋላ ደግሞ በሜሶጣሚያ ውስጥ ሰፈሩ ፡፡ በሰሜን ምዕራብ ትስታል በሰሜን ምዕራብ ትልቁ የቅድመ-ኮልበስያን ከተማ በአሁኑ ጊዜ በአርጀንቲና ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የ 2000 ነዋሪ ህዝብ ብዛት ያለው ነው ፡፡.36 የአርጀንቲና የአገሬው ተወላጆች ህዝቦች በሁለት ትላልቅ ቡድኖች ተከፍለው ነበር-አዳኞች እና ሰብሳቢዎች ፣ ፓፓጋኒያ ፣ ፓምፓ እና ቻኮ የኖሩት ፡፡ አርሶ አደሮቹ በሰሜናዊው በኩዮ ፣ በሴሬስ ደ ኮርዶባ እና በኋላ ደግሞ በሜሶፖታሚያ ሰፈሩ ፡፡ በሰሜን ውስጥ ትስታይል በአሁኑ ጊዜ በአርጀንቲና ግዛት 3000 ነዋሪዎችን የያዘችና በአሁኗ የአርጀንቲና ክልል ውስጥ የሚገኝ ትልቁ የቅድመ-ኮምቢያን ከተማ ነበረች። በዚህ ክልል ውስጥ የመጀመሪያዎቹ የሰዎች ሕይወት ትዝታዎች ከሶስት ሺህ ዓመታት በፊት የመጀመሪያውን የሜቶሊቲክ እና የኒዎሊቲክ ባህላዊ መዋጮን ካካተቱ የፓሊዮሎጂ ባህላዊ ደረጃዎች ጋር ይዛመዳል ፡፡ በሦስት ዋና ዋና ቡድኖች ሊከፋፈሉ ከሚችሉ የተለያዩ ማህበራዊ ድርጅቶች ጋር በተለያዩ የአገሬው ተወላጅ ሕዝቦች: እንደ ያጋን ወይም ያማና እንዲሁም በታይራ ዴል ፊውጎ እና በፌጂጂ ቻናሎች ያሉ መሰረታዊ የምግብ ውቅያኖስ ጀልባዎች አዳኞች እና አሰባሳቢዎች ፡፡ ፓፓፓኒያ ፣ ፓምፓ እና ቻኮ የኖሩ አዳኞች እና ሰብሳቢዎች እንደ ፓምፓይድ ያሉ የተራቀቁ አዳኞች እና የምግብ ሰብሳቢዎች-በማዕከላዊ ምስራቅ-በፓምፓ እና በሰሜን ፓትጋኒያን ክልል በሚገኙ ፕራግ እና ሬትሮዎች ውስጥ ቁሶች; እና ፓንጋኒያ ውስጥ ቾንችስ - ከ ጀምሮ ጀምሮ ወረራ ፡፡ በፓትጋኒያ ውስጥ ባለው የማፔቼ ሸክላ ሠራተኞች - እና በቻኮ ክልል ውስጥ ኩ እና ዊቺ የተባሉት የዚህ ቡድን አባል የሆኑት ፓምፓ እና ሚይንያን የተባሉት የሸክላ ስራዎችን ያካተቱ ናቸው። እንደ ጉዋኒ እና አንዲያን ያሉ የሴራሚክ ገበሬዎች እና የተገኙ ባህሎች ፡፡ ከሁለተኛው ሺህ ዓመት ጀምሮ አቫ (እስፓንያውያን “ጉራኒስ” በመባል የሚታወቅ) ከ 17 ኛው ክፍለዘመን ጀምሮ የሚታወቅ የአማዞን ህዝብ ኤአይአ እና የአርጀንቲና ሎቶ ወረራ። እነሱ እንደ ካሳቫ እና አቫት ወይም የበቆሎ በከብት እርባታ (ጫካዎች መቁረጥ እና የሚቃጠሉ) አርሶ አደሮች ነበሩ እና ስለሆነም ሰሜናዊው ክፍል በግብርና እና በከብት ላይ ያተኮረ ባህሎች በንጹህ ሰልፎች ነበሩ ፣ እናም በአሁኑ ጊዜ በተጠራው ቡድን ውስጥ የተካተቱ የንግድ መረቦችን ያዳበሩ ነበር ፡፡ "ኮችዋዋ"; በአካባቢያቸው ጌቶች ዙሪያ የ ሥርዓት ካቋቋሙ በኋላ በ 1480 ዓ.ም. በኢናካ ግዛት ተቆጣጠሩ ፡፡ በእነዚህ የአንዲያን ባህሎች ተጽዕኖ ስር ያሉ ሌሎች ሰዎች ፣ እና አነስተኛ ልማት ግብርና እና የከብት ልማት ተገንብተዋል ፡፡ የአሁኗ አርጀንቲና እና የኩዮ መሃል የአፓርታማ እና የተራራማ አካባቢዎች ሁኔታ። በ 14 ኛው እና በ 15 ኛው ክፍለዘመን የኢንኮ ግዛት አሁን ያሉትን የጁጁይ ፣ ሳልታ ፣ ካታማርካ ፣ በጣም ሩቅ ምዕራባዊ ቱትራን አውራጃን ፣ ላውን ሪዮጃጃና እና ሳን ጁዋን የሰሜን ምዕራብ ግዛት ሰሜናዊ ምዕራብን ድል አደረገ ፡፡ ሞንዶዛ እና ምናልባትም የሰሜናዊ ሳንቲያጎ ዴል ኤስትሮሮ ግዛቶ ን የቱዋርትባኦ ደቡባዊ ክፍል ወይም የግዛቱ ግዛቶች ወደ ሆኑት ኮሱዮ በማካተት ይሆናል ፡፡ በተለምዶ ፣ ወረራ የሚከናወነው በኢንካ ንጉሠ ነገሥት ቱፋክ ዩፒንኩዊ ነው ፡፡ በክልሉ ውስጥ ያሉ በርካታ የጌትነት ጌቶች ፣ እንደ ኪቹቻስ ፣ መስኩዋናይ (አአካማ) ፣ ዋልድስ ፣ ዲያጉዋስ እና ሌሎችም ፣ ለመቃወም ቢሞክሩም ኢናስ በእነሱ ላይ የበላይነት ያላቸውን የቼቻ ነገዶች ወይም ከተባረረ ከ ነገዶች ፣ የአሁኑ የቦሊቪያ ክልል ደቡብ-ምዕራብ በሚባለው አካባቢ ይኖር ነበር። እንደ ሳውድ አከባቢዎች ፣ ሉሊት-ቶኖኮቴ እና ሄኒያ-ካሚር (ታዋቂው “ቀንድ አውሎን” በመባል የሚጠሩ) ያሉ ሌሎች ሰዎች የ ወረራ በተሳካ ሁኔታ በመቃወም ገለልተኛ ጌትነት ኖረዋል ፡፡ የግብርና እና የጨርቃጨርቅ ማዕከላት ፣ ሰፈሮች (ኮላካ እና ታምቦስ) ፣ መንገዶችን (“ኢንካ ባቡር”) ፣ ምሽጎችን (ፓካዎችን) እና ከፍተኛ የተራራ ሥፍራዎችን ፈጥረዋል ፡፡ አንዳንድ ዋናዎቹ የቲልካ ፣ የፓስካ ፣ የኢንካ ፣ የፓሉካ ፣ መቅደስ ፣ የሎንዶን ፍርስራሽ እና የኪልሜስ ፍርስራሾች ናቸው። የስፔን ወረራ እና ቅኝ ግዛት የስፔን ወረራ እና የአርጀንቲና ቅኝ ግዛት በ 16 ኛው ክፍለዘመን እና በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ መካከል ያለውን የስፔን ግዛት በተቆጣጠረበት እና ከተቆጣጠረበት የ 19 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ መካከል ያለውን ጊዜ ያመለክታል። በዚህ ጊዜ አርጀንቲና (ብሩ ሀገር) የሚለው አገላለጽ ከሪዮ ዴ ላ ፕላታ ወደ ሰሜን ምዕራብ የሚዘረዝር ድንበር ያለ ክልል ለመሰየም ለመጀመሪያ ጊዜ ብቅ ብሏል ፡፡ ይህ ጊዜ የስፔን ለመጀመሪያ ጊዜ የአርጀንቲና ግዛት ወደ ተለያዩ አካባቢዎች መምጣትን ያጠቃልላል ፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ የአገሬው ተወላጆች ቀደም ሲል ያንን ክልል የጠሩበትን ስምም በሌሎችም በአዲስ ስም ሰየማቸው ፡፡ በአርጀንቲና የቅኝ ግዛት ዘመን በሦስት ጊዜ ይከፈላል-ግኝት እና ወረራ ፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ የግዛቱ ፍተሻዎች እና ዋና ከተሞች መመስረት; የስፔን ሰፈሮች የአገሬው ተወላጅ በሆኑት ሕዝቦች ላይ ተዋግተው ጥቂት አካባቢዎችን እና ኢኮኖሚያዊ ለውጦችን በማስመዝገብ ማጠናቀር የሞከሩበት ገዥው ዘመን ፣ እና የስፔን ምክትል አባረረ እና የራስ-መንግስት ቦርድ እስከ ተሾመበት እስከ 1810 እ.ኤ.አ. ግንቦት 18 አብዮት ድረስ ያለውን የምክትል ጊዜ። የአርጀንቲና የነፃነት ጦርነት ብዙውን ጊዜ የአርጀንቲና ታሪክ አካል ተደርጎ ተጠቅሷል። አውሮፓውያን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዘመናዊው የአርጀንቲና ክልል የገቡት ሁዋን ዲ ዝ ደ ሶስ ወደ ሪዮ ዴ ላ ፕላታ ወረደ። በኋላ ፣ በ 1520 የፈርናን ደ ማሌላንሌስ ጉዞው በሳንታ ጁሊያን የባህር ዳርቻ ፣ በሳንታ ክሩዝ አውራጃ ዛሬ መርከቦቹን አግዶላቸዋል። ፎርት ሳንቴይቲ መንፈስ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሰፈር ሲሆን በ 1527 በፓራና ወንዝ ዳርቻዎች ላይ ተጭኖ ነበር ፡፡ የሰሜን ምዕራብ እና የአገሪቱ የመጀመሪ ፍለጋ በ 1543 እ.ኤ.አ. በሴኔዶ ዴ ሮጃስ መግቢያ ነበር ፡፡ የአሱሱኒ ፣ ሳንቲያጎ ዴል ኢስትሮ ፣ ኮሮዶባ እና ቡነስ አይረስ ነበሩ ፡፡ በሰሜናዊው የአርጀንቲና ግዛት ሰሜናዊ አጋማሽ ላይ የታገደ የቅኝ ግዛት ማቋቋም መሠረቶች በስፔን ዘውዴ (የሪዮ ዴ ላ ፕላታ አስተዳደር) ተገ ናቸው። የስፔን ግዛት በርካታ ከተሞችን ያቋቋመ ሲሆን እ.ኤ.አ. በ 1860 የአርጀንቲና ሪ ብሊክን ለመመስረት ከተመሠረቱት አሥራ አራት አውራጃዎች ጋር በሚመደበው ሕዝብ ላይ የቅኝ ግዛት ሕግ አወጣ ፡፡ በቅኝ ገዥው ዘመን ማብቂያ ላይ የስፔን ግዛት የሪዮ ዴ ላ ፕላታ ተተኪ ግዛቶችን እና የወቅቱን የቦሊቪያ ፣ የፓራጓይ እና የዩራጓይ ግዛቶች ግዛትን የሚያካትት የሪዮ ዴ ላ ፕላታ ምክትል ፈጠራን ፈጠረ። በ 1537 በፕሬስ ፖል ሦስተኛው የብሉሚሊስ ዴዩስ ቡልጋሪያ የአገሬው ተወላጅ የክርስትናን ተፅእኖ እና ችሎታ ሁሉ በማወጅ በአሜሪካ ውስጥ በስፔን ፣ በአንግሎ ሳክሰን እና በፈረንሣይ ቅኝ ግዛት መካከል ከፍተኛ ልዩነት ነበር ፡፡.42 በስፔን ግዛት ውስጥ ማህበራዊ አንድነት የተካሄደው በካቶሊክ ቤተክርስቲያን እምነት አንድነት ነበር ፡፡ የቅኝ ግዛት በአንደኛው ክፍለ ዘመን የስፔን ግዛት የአሁኑን የአርጀንቲናን ግዛት አንድ ሦስተኛ ያህል ድል በማድረግ ነዋሪዎ ን ለሚኖሩት ሕዝቦች የመጀመሪያ ተገዥ በመሆን የስነ ሕዝባዊ ጥፋት አመጣ ፣ ለዚህም ነው የአውሮፓ ድል አድራጊዎች የተጠለፉ ባሮችን በጥቁር አፍሪካ ውስጥ አስገቡ ፡፡ በ 17 ኛው ክፍለዘመን የጁኢት ጓራኒ ተልእኮዎች የተቋቋሙት በጊራኒ እና በተዛመዱ ህዝቦች መካከል በኢየሱስ ማህበር የተቋቋሙት የሚስዮናውያን ማህበረሰቦች ነበር ፣ እነዚህ የአሁኖቹ የአገሬው ተወላጅዎች ባርነት በወንጌላዊነቱ ፣ በአገሬው ተወላጆች እና በፓራጓይ ክፍል የሚገኙትን ለመከላከል ነው ፡፡ እና ብራዚል ሥራቸውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቅቀዋል ፡፡ እ.ኤ.አ. እስከ 1768 ድረስ የስፔኑ ንጉሥ ካርሎስ ሦስተኛው ኢየሱሶችን አባረረ ፡፡ የአሁኑ የአርጀንቲና ክልል እና ነዋሪዎቹ የአገሬው ተወላጅ ሕዝቦች በስፔን በቅኝ ግዛት ስር አልነበሩም ፣ በተለይም በቻኮ (በቺቺ እና በኬም) እና በፓምፓን-ፓፓጋኒያን (በቱሁቼ-ማቼ-ራኳል) ክልሎች ስር። . እ.ኤ.አ. ከ 1560 እስከ 1667 መካከል ባለው የወቅቱ አርጀንቲና ሰሜን ምዕራብ ውስጥ የካልኩኪ ጦርነቶች የሚባለውን የካልኩኪ ጦር መርከቦች በመባል የሚታወቁትን ጠንካራ ተቃውሞዎች ጠብቀዋል ፡፡ በአብዛኞቹ የቅኝ ግዛት ጊዜያት የአርጀንቲና ግዛት የፔሩ ምክትል አካል ነበር ፣ እስከ 1776 ድረስ የስፔን ንጉሥ ካርሎስ ካርሎስ ሦስተኛው ግዛቱ ሪዮ ዴ ላ ፕላታ ከሚባል ክልል ጋር እስኪተካ ድረስ። የቦነስ አይረስ ከተማ እንደ የንግድ ማእከል እያደገች በመሄ እና በተቻለ መጠን የፖርቱጋልን ጥቃት በተሻለ መቃወም እንዲሁም በቀላል ተደራሽነት በመገኘቷ ዋና ከተማዋ ሆነች ፡፡ እስፔን በአትላንቲክ ዳሰሳ በኩል ፡፡ በ 18 ኛው ክፍለ ዘመን የዱር ከብቶች ተፈጥሮአዊ መባዛት እና በፓምፓ ማሳዎች ፣ በምስራቃዊ ሪዮ ደ ላ ፕላታ እና በደቡባዊ ብራዚል ውስጥ ፈረስ ተብሎ በሚጠራ ፈረስ ላይ ልዩ ገለልተኛ ገበሬ እንዲመስል ምክንያት ሆኗል ፡፡ ለወንዶች እና ለቻይና በሴቶችም ፡፡ ጋውቾዎች የራሳቸውን ባህርይ ያዳበሩ ባህል ነበራቸው ፣ በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛ አጋማሽ እስከሚሸነፍ ድረስ የእንስሳትን እና የመሬትን የመጠቀም መብታቸውን ለማስጠበቅ የእራሳቸውን ባህሪዎች ባህል አደረጉ ፣ ተዋግተው ተዋግተዋል ፡፡ ይህ በዱር እንስሳት ውስጥ ያለው ይህ ሀብታም ከስፔን እና ክሪዮል ህዝብ ጋር የእንስሳት ሃብት የማይለዋወጥ ትግል የጀመረው በቻኮ ፣ ፓምፓ እና ፓራሲታኒያ ውስጥ የአገሬው ተወላጅ የእኩልነት ባህል እንዲታይ ምክንያት ሆኗል። እስከ አሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ አብዛኛው ፓፓጋኒያ እና ፓምፓስ በተለያዩ የአገሬው ተወላጆች ቁጥጥር ሥር ነበሩ-በዋነኝነት ቾንኬኮች እና ከዚያም በፓትፓኒያ ውስጥ ያሉት ማች እና በፓምፓስ ሜዳዎች እስከ አሥራ ዘጠነኛው ክፍለ-ዘመን የመጨረሻ ሩብ ድረስ። በተመሳሳይም አብዛኛው የቻኮ ክልል ግዛቶች በአውሮፓውያን ቅኝ ግዛት አልነበሩም ፣ ነገር ግን እንደ ኪም ፣ ሞኮቭስ (ሞኮቪስ ወይም ሞኮቪስ) ፣ ፒላጊስ እና ቺስ እስከ 20 ኛው ክፍለዘመን መጀመሪያ እስከሚጀምሩ ድረስ ተወስደዋል። የሚዘናጉ የአገሬው ተወላጆች ቁጥር በስፔን ሕዝብ ላይ በቋሚ ጥገኛ ግንኙነቶች ተገፍቷል ፡፡ ምንም እንኳን በትውልድ ትውልድ ሲያልፍ ምንም እንኳን እንደ “ክሪዮል” በሚባል የብሔራዊ መለያ ቁጥር ቢቆጠርም ፣ ይህ የክትትል ሂደት በአጠቃላይ በሰሜን ምዕራብ የአርጀንቲና ክልል ውስጥ ከፍተኛ የሕዝብ ተወላጅ ተሳትፎ በ 1780 ከታሪካዊ ክልል ጋር የተሳተፈ በመሆኑ የተረጋገጠ አይደለም ፡፡ በኢንካ ቱፋክ አማሩ የሚመራው ኩዙኮ። በአርጀንቲና ታሪክ እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በ 1810 እ.ኤ.አ. በግንቦት 18 አብዮት መካከል እና ሁሉንም ብሔራዊ ባለስልጣናት ባጠፋው አና መካከል መካከል የዘለቀ የነፃነት ዘመን በመባል ይታወቃል ፡፡ በዚህ ወቅት የተባበሩት የተባበሩት የሪዮ ዴ ላ ፕላታ የአሁኑ የአርጀንቲና ሪ ብሊክ የመጀመሪያ ስማቸው - ሉዓላዊ ሀገር በመሆን ህልውናቸውን የጀመሩት በተራዘመ የነፃነት ጦርነት አማካኝነት በተሳካ ሁኔታ ድጋፋቸውን በመግለጽ ነፃነታቸውን አወጁ ፡፡ ግን በዚህ ጊዜ ውስጥ እራሳቸው በቋሚነት በሁሉም ግዛቶቻቸው ተቀባይነት ያገኙ ማዕከላዊ መንግስት እና ህገ መንግስት አልሰጡም ፡፡ በተጨማሪም በዚህ ወቅት ነበር የሪዮ ዴ ላ ፕላታ ምክትል አካልነት ከአርጀንቲና ተለይተው የተለያዩባቸው ግዛቶች ፤ ፓራጉዋይ ፣ የራሳቸውን በራስ የመመራት ሂደት በመደገፋቸው። የላይኛው ፔሩ ፣ ከስፔን ኃይል ስር ለመቀጠል ፣ በኋላም እንደ ቦሊቪያ ሪ ብሊክ ነፃ የምትሆንበት ፡፡ እና የምስራቅ ባንድ ፣ ከብራዚል ይወርሷታል ፣ እናም እንደ ምስራቃዊ የኡራጓይ መንግሥት ገለልተኛ ትሆናለች ፡፡ የወቅቱ መጀመሪያ የተቋቋመው የተባበሩት መንግስታት ግዛቶች የመጀመሪያው መንግስት የተፈጠረበት ቀን እና የካቲት 11 ቀን 1820 የመጨረሻው የካቲት (እ.አ.አ) የመጨረሻ የበላይ ጠቅላይ ሥራ አስፈፃሚ ሆሴ ሮዴን ለቅቆ ሲወጣ ነው ፡፡ ብሄራዊ ኮንግረስ ፡፡ የመጀመሪያ የበላይ ቦርድ በሪዮ ዴ ላ ፕላታ ስም የመጀመሪያው የሪፖርት ቦርድ በይፋ የሪዮ ዴ ላ ፕላታ ስም የሆነው ሚስተር ዶን ፈርናንዶ ስድስተኛ አርብ ግንቦት 25 ቀን 1810 እ.ኤ.አ. ፕሌታ ፣ ምክትል ቦልዛር ሂሊጎ ደ ሲኔኔሮ የተባረረ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት የዩኒቨርስቲዎች የመጀመሪያ ቦርድ ፕሬዝዳንት ሆነው የሾሙት ሜይ አብዮት ድል እ.ኤ.አ. የመንግስት መቀመጫ የተቋቋመው በቦነስ አይረስ ፎርስ ውስጥ ሲሆን ፣ እ.ኤ.አ. ከ 1776 ጀምሮ የምክትል መስሪያ ቤቶች መኖሪያና የመንግሥት መስተዳድር በሚገኝበት የመንግሥት አዳራሽ ተቋቁሟል ፡፡ የመጀመሪያው ቦርድ እ.ኤ.አ. እስከ ታህሳስ 18 ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ ኖሮት ነበር ፣ ምክንያቱም ከውስጡ የውክልና ሃላፊዎችን በማካተት ለሪዮ ዴ ላ ፕላታ ማራዘሚያ ለረጅም ጊዜ የዘለቀ የነፃነት ጦርነት ያስመዘገበው ትልቁ ቦርድ ሆነ ፡፡ ከስፔን ፡፡ የነፃነት ጦርነት እየተስፋፋ በነበረበት ጊዜም በ 1814 የእርስ በርስ ጦርነት መጀመሪያ ላይ በተነሳው እና በቋሚነት ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ የሚቆየውን የአዲሲቷ አዲስ መንግስት አወቃቀር ውዝግብ አስነስቷል ፡፡ የፌዴራል ክፍልፋዮች መሪ ፣ የምሥራቃዊ ጆሴ ገርቫሺዮ አርጊስ የነፃ ህዝቦች ህብረት ጠበቃ ፣ በቡኤነስ አይሪስ የመተዳደር እምቢተኛ የክልሎች ሊግ ተብሎ ተጠርቷል ፡፡ ኮንቴፔሲዮን ዴ ዩራ ኡራጓ የተባለ የምስራቅ ኮንግረስን አደራጅቷል ፣ ይህም የስፔን ገለልተኝነቱ እንደተገለፀው አሁንም ድረስ ማወጅ መቻሉን ወይንስ ክርክር አከራካሪ ነው ፡፡ እ.ኤ.አ. ሐምሌ 9 ቀን 1816 በሳን ሚጌል ደ ቱከም ከተማ ውስጥ ፣ በሰሜን ምዕራብ እና በማእከላዊ ምዕራባዊ የአገሪቱ ክልሎች የተወካዮች ምክር ቤት እና ከቡነስ አይረስ የተወሰኑት ከከፍተኛ ፔሩ ከተባረሩ የተወሰኑ ተወካዮች ጋር ተሰብስቧል ፡፡ የሚከተሉትን ቀመር በመጠቀም በደቡብ አሜሪካ የተባበሩት መንግስታት ግዛቶች ነጻነት ፡፡ የተሰረቁትን መብታቸውን ይመልሳሉ ፣ እናም ነፃ እና ገለልተኛ በሆነው የንጉሥ ፈርዲናንድ ፣ ተተኪዎቹ እና የከተማ " በደቡብ አሜሪካ የተለያዩ አካባቢዎች አዲሶቹ መንግስታት በክልሉ ውስጥ ያለውን የስፔን ንጉሣዊ ስልጣን ለማስመለስ የሚሞክሩትን የንጉሣዊያን ወታደራዊ ተቃራኒዎችን መቋቋም ነበረባቸው ፡፡ ለነፃነት ጦርነቶች ተጀመሩ ፡፡ የአንዳንድ ዋና አዛች ሰሜናዊ ጦር ሰራዊት አዛዥ የሆኑት ሆሴ ዴ ሳን ማርቲን የተባሉ የአንዲስ ጦር ሠራዊት ፈጣሪ ፣ ማርቲን ሚጌል ደ ጎሜዝ ፣ የጎጃው ጦርነት አዘጋጅ እና ጁና አዙሩዲ የተባሉ የጦር ኃይሎች ጦር አዛዥ የነበሩ ናቸው ፡፡ አልቶ ፔሩ. የአርጀንቲና ግዛት ሳን ማርቲንንን እንደ ነፃነቷ ታላቅ ወታደራዊ ጀግና እንደሆነች በመቁጠር “የአባት አባት አባት” የሚል ማዕረግ አከብረዋታል። ከሲሞን ቦሊቫር ጋር በመሆን ፣ በአህጉሩ ላይ የስፔን መኖር ለተቋረጠው የነፃነት ሥራዎች ሀላፊነታቸው ነበሩ ፡፡ የፌዴራል መንግሥት መቋቋም የመጀመሪያዎቹ ዐሥርት ዓመታት ገለልተኛ አገር እንደመሆናቸው ግጭት ተጋርጦ ነበር-የዩኒተርስታዎችን ቅርስ በመጋፈጥ የፌደራል ፌዴሬሽኑ በተደጋጋሚ የየክልሎች ነፃነቶችን በመጠበቅ ይነሳሉ ፣ ይህም ከዓመቱ ኤክስሲ ተብሎ የሚጠራው - የአገሪቱ ክፍል ወደ በራስ-ገዝ ግዛቶች መከፋፈል ይመራል ፡፡ አገሪቱ በ 1825 እና በ 1827 መካከል ለአጭር ጊዜ ብቻ የምትቆይ አገር ብትሆንም በወታደሮች መሪዎች እስከ 1852 ድረስ የመንግሥት መንግሥት አልነበራትም ፡፡ የነፃነት ጦርነት እስከ 1825 ድረስ የቀጠለ ሲሆን በሰሜን ድንበር እና በፔሩ ግን በተሻለ ሁኔታ ተዋግቷል ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ምስራቃዊው አውራጃ በፖርቱጋል መንግሥት ወረራ ከነበረችበት ወደ ብራዚል መንግሥት ተሻገረ ፡፡ በዚህ የተነሳ የተከሰተው የብራዚል ጦርነት እ.ኤ.አ. በ 1828 በቀዳሚ የሰላም ስምምነት የተፈረጀውን ፣ በምስራቃዊ የኡራጓይ ግዛት ስም የተጠራጠረውን ክልል ገለልተኛ በሆነ በይፋ ባወጀው እ.ኤ.አ. በ 1825 የላይኛው ፔሩ የቦሊቪያ ሪ ብሊክን ተቋቋመ ፡፡ ቀጥሎም የታራጃ ከተማና ግዛቱ ታከለ ፡፡ በተሻሻሉ ወታደራዊ ዘመቻዎች በሕንዶቹ ላይ የተካሄደ ዘመቻን በተወሰነ መጠን ከፍ ለማድረግ የረዳው ቀሪ ክልል በ 1820 ዎቹ አጋማሽ በይፋ ‹አርጀንቲና› የሚለውን ስም መጠቀም ጀመረ ፡፡ ዴ ላ ፕላታ በሕገ-ወጥነት ወደቀ ግን ቢሆንም በአገሪቱ ሕገ-መንግስት እንደ ሀገር አማራጭ ስም መጠቀሱ ቀጥሏል። እ.ኤ.አ. በ 1830 ዎቹ መጀመሪያ የአርጀንቲና ኮንፌዴሬሽን ስም የተሰየመ ዝንቦች በመላው አገሪቱ ስኬታማ ሆነዋል ፡፡ ከሃያ ዓመታት በላይ የቦነስ አይረስ የፌዴራል ገዥው ጁዋን ማኑኤል ደ ሮዛ በእውነቱ ከፍተኛውን ብሔራዊ ባለሥልጣንን ይገምታል ፣ ምንም እንኳን በንድፈ ሀሳብ ምንም እንኳን የክልሎች የውጭ ወኪሎች የውጭ ወኪል ብቻ ቢሆንም ፡፡ በግርማዊ ቀዳማዊ አ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ፣ ተከታታይ የክፍለ-ጊዜ አመፅዎችን ፣ እንዲሁም የፈረንሳይ ሪዮ ዴ ላ ፕላታ እና ከዚያም የታላቋ ብሪታንያ እና የፈረንሳይ የጋራ ድንበር ተዋግቷል ፡፡ እንዲሁም በፔሩ-ቦሊቪያ ኮንፌዴሬሽን እና በኡራጓይያ ዋና ከተማ በሆነችው በሞንቴቪዲ በተባለችው የመከላከያ መንግሥት በተባበሩት የአርጀንቲና የእርስ በእርስ ጦርነትዎች መካከል የተደረጉ ግጭቶች ነበሩት ፡፡ ሊተገበር የሚችል ሰላም ቢኖርም እና በሊቶራል አውራጃዎች ውስጥ ቢያንስ ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ የሮዝያስ ጠላቶች በ ገዥው የጠፋውን የግለሰቦችን ፣ የፖለቲካ እና የመግለጫ ነፃነቶችን ጠይቀዋል ፡፡ የይገባኛል ጥያቄዎ ዋነኛው አገራዊ መንግስትን የሚያደራጅ እና የዜጎችን መብት የሚያረጋግጥ የፖለቲካ ህገ-መንግስት ማዕቀብ መጣል ነበር ፡፡ ብሔራዊ ድርጅት እ.ኤ.አ. በ 1852 ሮዛስ በ ጦር ፣ በኢሬሬ ሪዮ ግዛቶች እና በቀሪዎቹ የኡራጓይ እና ሌሎች የብራዚል ቀይሮች መካከል ጥምረት የሆነው የሮዛስ ጦርነት በ ድል ተነሳ ፡፡ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንቱን በበላይነት የሚመሩት የኢሬሬ ሪዮ ገዥው የፌዴራል የፀረ-ሽብርተኛ ጁሱ ሆሴ ደ ኡራኪዛ ቡድን ግንባር ቀደም ነበር ፡፡ ከአንዳንድ ለውጦች ጋር እስከ ዛሬ ድረስ አገሪቱን ሲገዛ የቆየው ሕገ መንግሥት እስከሚሠራበት ጊዜ ድረስ በ 1853 ነበር ፡፡ የፌዴራሉን መንግሥት ተቀበለ ፣ ግን የቦነስ አይረስ ግዛት ዋና ከተማዋን በፓራን ከተማ መመስረት ካለባት ከአርጀንቲና ኮንፌዴሬሽን ተለየች ፡፡ እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በ 1859 ኮንፌዴሬሽን በሴፔ ጦርነት ቡናን አይኤስ ተብሎ የሚጠራውን የሳን ሆሴ ደ ፍሬስ ስምምነትን እንዲፈርም በማስገደድ እ.ኤ.አ. በ 1859 እ.ኤ.አ. ሆኖም በቡሮሞን ሜየር ሊቀመንበር ወቅት በፓን ጦርነት (እ.ኤ.አ. 1861) በኋላ በቡነስ አይረስ መሪነት የመጨረሻው ውህደት ተገኘ ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1865 አርጀንቲና እንደገና በኡራጓይ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ገባች ፣ የፓራጓይ ከተማዎችን በቁጥጥሩ ስር በማድረግ ፓራጓይ ምላሽ ሰጡ ፡፡ አርጀንቲና ከብራዚል እና ከኡራጓይ ጋር የሶስትዮሽ ጥምረት ከፈረመች በኋላ አርጀንቲና አምስት ዓመታትን ያስቆጠረና አሥር ሺህ የአርጀንቲና ወታደሮችን ተሳትፎ የሚጠይቅ የሶስትዮሽ ህብረት ጦርነት ተካሂ .ል ፡፡ የወንዶቹ አብዛኛው ክፍል ሙሉ በሙሉ ወድሟል እና ሞቷል በአርጀንቲና ውስጥ የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲነሳ ምክንያት የሆነው እጅግ በጣም ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እና የሰው ሕይወት ቢኖርም ፣ ይህች ሀገር በሰሜን ምስራቅ ድንበሯን ማጠናከር ችላለች ፣ ድንበሩ በፒሊሴሲ ፣ ፓራጓይ እና በፓራና ወንዞች ውስጥ ነበር የተደረገው። በሚርተር አስተላላፊዎች እና በተለይም የሳርሚንቲኖ እና አላላንዳ አርጀንቲና በትልቁ የባቡር አውታር እና የትምህርት ሥርዓቱ እድገት በሚታደግበት የዓለም ኢኮኖሚ እራሷን በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ አስገባች ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1874 እና በ 1880 ከሁለት የደም ካደጉ በኋላ በዚህ ዓመት ባለፈው ዓመት የቦነስ አይረስ ከተማ በፌዴሬሽኑ የተዋቀረች ሲሆን በክልሎችና በዋና ከተማው መካከል ዘላቂ ሚዛን ተፈጠረ ፡፡ ወግ አጥባቂ መንግስታት እና የመጀመሪያዎቹ ሥር ነቀል መንግስታት በ 1878 እና በ 1884 መካከል የድንበር እና የቻኮ ውድድሮች በመባል የሚታወቁት በአገሬው ተወላጅ እና በክሬምለሎች መካከል የማያቋርጥ ግጭቶችን ለማቆም እና በአገሬው ተወላጅ ግዛቶች ላይ አግባብነት ያላቸውን ተጓዳኝ ግዛቶች እንዲመደቡ ለማድረግ ነበር ፡፡ ጁሊ ኤ ሮካ ያስተዋወቀው የመጀመሪያው ወረራ በዋናው ህዝብ ቁጥጥር ሥር ወደተባበሩት ፓምፓሶች እና ፓትጋኒሺያ ግዛቶች ተከታታይ ወታደራዊ ወረራዎችን ያቀፈ ነበር ፣ እናም የጉዞው ባለሀብቶች የገጠር ማኅበረሰብ አባላት ውስጥ ይከፋፍሏቸዋል። እስከ ምዕተ ዓመቱ መገባደጃ ድረስ በብሔራዊ ኢኮኖሚ ስርዓት ውስጥ የተካተተው ሙሉ ውህደቱ የተከናወነው ከእንጨት እና ታኒን ምርት የተወሰደው በጥጥ በማምረት ሲተካ ብቻ ነው ፡፡ የአርጀንቲና መንግስት እንደ ክሪዮስ እና አውሮፓውያን ተመሳሳይ መብቶች ሳይኖር የአገሬው ተወላጅን እንደ አናሳ ፍጡራን አድርጎ ይመለከታል። እ.ኤ.አ. ከ 1880 እስከ 1916 ባለው ጊዜ ውስጥ በብሔራዊ በራስ ገዝ ፓርቲ (ፒኤን) በዘፈን ምርጫ ስርዓት መሠረት ስልጣንን በመጠቀም ሥልጣኑን ተረከበ እና ለ 25 ዓመታት ብቸኛው ሰው ጄኔራል ጁሊዮ አርጀንቲና ሮካ ነበር ፡፡ ወይም ተብሎ የሚጠራው በብሪታንያ ግዛት በወጣው ዓለም አቀፋዊ የሥራ ስምሪት የሠራተኛ ክፍፍል ላይ በመመርኮዝ ስኬታማ እና ዘመናዊ የግብርና ኤክስፖርት ሞዴልን አደራጅቷል ፡፡ በባህላዊው መለያ ሀገር በዚያን ጊዜ “የዓለም ዳቦ መጋገሪያ” ሆና ታየች ፡፡ ይህ ኢኮኖሚያዊ ሞዴል በጥቂት እጆች ውስጥ የሀብት ክምችት እንዲገኝ ከማድረጉ እና ከፓምፓስ ክልል ውጭ ያሉ የሰራተኛ የሥራ መደቦች እና ህዝቦች ማህበራዊ መገለል እንዲፈጠር አድርጓል ፡፡ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ ወደ አንድ ትልቅ የኢሚግሬሽን ፍሰት ደረጃ ላይ በመድረሱ በዋናነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ጣሊያናውያን እና ስፓኖችን ያቀፈ ሲሆን የምስራቅ አውሮፓውያን እና የምዕራባዊያን እስያዎችን ተከትሏል ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1869 ከዓለም ህዝብ 0.13% የተወከለው የአርጀንቲና ህዝብ እ.ኤ.አ. በ 1930 0.55% ይወክላል ፣ ይህ መጠን ከዚያ ጊዜ ወዲህ የተረጋጋ ይሆናል ፡፡ የኢኮኖሚው ብልፅግና አብዛኛዎቹ ስደተኞች ወይም ዘሮቻቸው የሆኑትን አንድ በጣም መካከለኛ የመካከለኛ ደረጃ ዕድገት አስነስቷል ፡፡ የአውሮፓውያን ስደተኞችም እንዲሁ ሶሻሊዝም እና የሀገር ውስጥ ቅኝ ግዛት ያሉ አዲስ የፖለቲካ ሀሳቦችን አስተዋውቀዋል ፣ እንዲሁም ከአከባቢው ህዝብ በተለይም ከአፍሮ-አርጀንቲና ጋር በጋራ መረዳጃ ድርጅቶች እና ማህበራት በመፍጠር ተሳትፈዋል ፡፡63 ዘመናዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ብቅ አሉ ፡፡ እንደ ራቲካል ሲቪክ ህብረት () እና ሶሻሊስት ፓርቲ (ፒ.ሲ.)። ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የፖለቲካ እና ማህበራዊ ግጭቶች ፣ የምርጫ ማጭበርበሮች እና ከባድ የጭቆና ድርጊቶች በኋላ ፣ ሴኔዝ ፔና ህግ በ 1912 ተተላለፈ ፣ ይህም ለወንዶች ድምጽ አሰጣጦች ምስጢራዊ ፣ አስገዳጅ እና ሁለንተናዊ በቂነት እንዲመሰረት አደረገ ፡፡ በድብቅ በቂ በሆነ የመጀመሪ የፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ወቅት ወግ አጥባቂዎች ከ1916 እስከ 1922 እና በ 1928 መካከል ፕሬዝዳንት በነበረው ሂፖሎ ዩሪ በሚመራው አክቲቪስቶች ከስልጣን ተፈናቅለው ነበር ፡፡ በአሰቃቂ ሳምንት እና በአመፀኛው ፓትጋኒያ የተፈጸመውን እልቂት ያመጣ ዩኒቨርስቲ እ.ኤ.አ. በሁለቱም የዩሪጊየን መንግስታት መካከልም አክራሪው ማርሴሎ ቶርኮቶ ደ አልር ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ፡፡ በኩፖት ዴታ እና በዲሞክራሲያዊ አገዛዞች መካከል አማራጭ እ.ኤ.አ. መስከረም 6 ቀን 1930 በአርጀንቲና የአርጀንቲና ወታደራዊ ቡድን ሂፖሎ ዩሪ ከተገለበጠ በኋላ አምባገነናዊ አገዛዙን ለማቋቋም በወሰነ ጊዜ መስከረም 6 ቀን 1930 ተከስቶ ነበር ፡፡ ይህ መፈንቅለ መንግስት አንፀባራቂ ዲዳ በመባል ለሚታወቁ የማጭበርበር መንግስታት ቅደም ተከተል አስነሳ ፡፡ የአርጀንቲና -ወደ ውጭ መላኪያ ሞዴል በ 1929 በተከሰተው ቀውስ ምክንያት በዓለም አቀፍ ገበያዎች መዘጋት ምክንያት ወደ ቀውስ ውስጥ ገባ ፡፡ አገሪቱ ሰፊ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ያደገች የማስመጫ የመተካት ሂደትን ከፍ አድርጋ ነበር ፡፡ የሁለተኛ መፈንቅለ መንግስት መፈንቅለ መንግሥት ወታደራዊ መንግስት የገባበት በዚህ ጊዜ ውስጥ በሠራተኛ ማህበራት እና በፔሮኒዝም ለተነሳው አንዳንድ ወታደሮች መካከል ህብረት ይከናወናል ፡፡ ይህች ሀገር በ 1941 መገባደጃ ላይ በጃፓን ጥቃት በተሰነዘረበት ወቅት አሜሪካ ከአሜሪካ ግፊት ቢገጥምም አርጀንቲና በአብዛኛዎቹ የዓለም ሁለተኛው ጦርነቶች ሚያዝያ 27 ቀን አጋቾቹን በመቀላቀል ገለልተኛ ሆነች ፡፡ ጦርነቱ ከመጠናቀቁ ጥቂት ቀደም ብሎ በጄኔራል ኤድልሚሮ ፋረል መንግሥት እ.ኤ.አ. ማርች 1945 ፡፡ እ.ኤ.አ በ 1946 ሁዋን ዶንጎን ፔኖ በሠራተኛ ፓርቲ ውስጥ የተደራጁ የሠራተኛ ማህበራት ድጋፍ በመሆን ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ ፡፡ ፔርኒ ከባለቤቱ ኢቪታ ጋር በመሆን ፣ የማህበራዊ ፍትህ ፣ የፖለቲካ ሉዓላዊነት እና የኢኮኖሚ ነጻነት ላይ አፅን ት የሚሰጥ አዲስ እንቅስቃሴን አመሩ ፡፡ በእሱ መንግሥት ውስጥ የሴቶች መሻሻል በ 1947 ተቋቋመ ፣ በቤተሰብ ሕግ ውስጥ የወንዶች እና የሴቶች እኩልነት ፣ በጋብቻ ውስጥ የተወለዱ ሕፃናት እኩልነት ፣ ነፃ የዩኒቨርሲቲ ትምህርት ፣ የወባ በሽታ ፣ ወዘተ ፡፡ በኢቫ ፔሮን ፋውንዴሽን አማካይነት በአገሪቱ ውስጥ ታይቶ የማያውቅ ማህበራዊ ድጋፍ የተገነባ ሲሆን ይህም የገንዘብ ተጋላጭ ለሆኑ ዘርፎች የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ነበር ፡፡ የባቡር ሀዲድ እና የውጭ ንግድም እንዲሁ በሀገር ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ከባድ ኢንዱስትሪን የሚያበረታታ ጠንካራ የኢንዱስትሪ ልማት የመነጨ ነበር ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1951 ፔሮን በአርጀንቲና ውስጥ ለወንድ እና ለሴቶች ሁለንተናዊ መሻሻል በሚደረግበት የመጀመሪያ ምርጫ ውስጥ 40% ድምጽን ለአዲስ ፕሬዝዳንትነት ምርጫ ተመረጠ ፡፡ በ 1952 ኢቪታ ሞተ ፡፡ ከ 60 ዓመታት በኋላ ፣ ቤንሴሜንታዊቷ ሴት በአርጀንቲና ታሪክ ውስጥ የሴቶች ሚና ምልክት ሆኖ ታወጀ ፡፡66 የሕዝቡን ሰፊ አድማጭ ነበረው ፣ ግን ደግሞ የተቃዋሚ ዘርፎችን ጠንካራ እምቢተኝነት ፣ የአርጀንቲና ማህበረሰብ በፔሮኒስቶች እና በፀረ-ፈረንሳሾች ውስጥ ፡፡ የእሱ ፖሊሲ የብሪታንያ ፍላጎቶችን የሚጎዳ ሲሆን በዚያን ጊዜ ተቃዋሚዎችን የሚደግፈው በኢኮኖሚ የበላይነት እስከሚገኝበት ጊዜ ድረስ ነው ፡፡ ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋር የተፈጠረው ግጭት የተጀመረው ለሰፋፊ መስሪያ ቤቶች መንግስት ያለው ታማኝነት እንዲዳከም እና ተቃዋሚዎችን አንድ አድርጎታል ፡፡ እ.ኤ.አ. ሰኔ 16 ቀን 1955 እ.ኤ.አ. በፕላዛ ዴ ማዮ እና በሌሎች ቦታዎች በቦነስ አይረስ የተባሉትን የቦነስ አይረስ የቦንብ ፍንዳታ በመጠቀም በጥይት የተከሰሱ 308 ተጎጂዎች ሴራ - ሲቪል-ወታደራዊ ሴራ ፡፡ 23 ሴቶችን ጨምሮ 111 የሰራተኛ ንቅናቄዎችን ጨምሮ - በሽንፈት ምክንያት ሊታወቅ ያልቻለው ሞት እና ከ 700 በላይ የሚሆኑት ጉዳቶች ተገኝተዋል ፡፡ እ.ኤ.አ. በመስከረም ወር ንዮን “ፉሺላራራ አብዮት” የሚል ቅጽል ስም የተሰየመ መፈንቅለ መንግስት የጀመረው ፔሮኒዝም ን የገደለበትን “ነፃ አውጭ አብዮት” በሚል ስያሜ በተሰየመ አዲስ መፈንቅለ መንግስት ተገለበጠ ፡፡ ንዮን በ 1973 እገዳው እስኪያበቃ ድረስ በግዞት ተገዶ ነበር ፡፡ በእገዳው ወቅት ሮኒዝም በፖለቲካ እና በንግድ ህብረትነት ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩ ይቀጥላል - ይህም ብዙ ምርጫዎችን ያሸነፈበት አካባቢ - ሕገ-መንግስታዊ ባልሆኑ መንገዶች የተሾሙትን ባለሥልጣናት ሕጋዊነት በመካድ እና በመቋቋም ላይ የሚታወቅ ተቃራኒ እንቅስቃሴን በማዳበር ላይ ይገኛፈረንሳዊ. እ.ኤ.አ. በ 1958 ፕሬዝዳንት አርቱሮ ፍሬሮዚዚ (ዩሲአይአይ) በፔሮንኒዝም ምርጫ ታግደው ነበር ነገር ግን እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. ከፔን ጋር የምርጫ ስምምነት ከደረሱ በኋላ እ.ኤ.አ. በ 1962 በተካሄደው አዲስ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ተገለበጡ ፡፡ ፍሮ ከተሰረዘ እና ከተያዘ በኋላ በዚያው ቀን በሹመት የስልጣን ክፍፍል ክስ በመሰንዘር የፍትህ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ሲቪያ ሆሴ ማሪያ ጉዲ ናቸው ፡፡ ምንም እንኳን ጊዲ በፕሬዚዳንታዊነት መደበኛ ስልጣን ብትይዝም እውነተኛው የቁሳዊ ሀይል በወታደራዊ መስሪያ ቦታ ላይ ትገኛለች ፡፡ በስልጣን ዘመኑ አዙሌ እና ኮሎራዶ በመባል በሚታወቁ የአርጀንቲና ጦር ጦርነቶች መካከል ያሉ ግጭቶች ተባብሰው ወደ ትጥቅ ግጭቶች ይመራሉ ፡፡ የ “ሰማያዊ” ክፍሉ ድል ጄኔራል ጁዋን ካርሎስ ኦንጋኒ ጦርን መልሶ ለመቀላቀል አስችሎታል ፡፡ ሮኒዝም አሁንም ታግዶ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ፍሬሮይዚ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ፣ እ.ኤ.አ. በ 1963 አርቱሮ ኡምቤርቤሊያ ኢሊያ () ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ ፤ እ.ኤ.አ. በ 1966 መንግስትን ወደ ኦንግጋኒያ የሚወስድ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ይወገዳል ፡፡ የእራሱ አምባገነናዊነት የራስ-ቅጥ ያለው የአርጀንቲና አብዮት (እ.ኤ.አ. 1966-1973) ከተመሰረተው የመጀመሪያው የሆነው ፣ እንዲሁም በላቲን አሜሪካ ከዩናይትድ ስቴትስ አማካይነት ጋር በመተባበር በጦር ኃይሎች ማዕቀፍ ውስጥ የተጫነ የመጀመሪያው ቋሚ አምባገነንነት ነበር ፡፡ የቀዝቃዛው ጦርነት ዓለም አቀፍ ማዕቀፍ የአሜሪካውያን ትምህርት ቤት እና የብሔራዊ ደህንነት አስተምህሮ። የፖለቲካ እንቅስቃሴን እና የመንግሥት ሽብርተኝነትን መሰረዙ እንደ ሞንቴሮንሮስ ፣ ኤአርአር እና ኢ.ፓ.ፒ. ያሉ በርካታ የደፈጣ ተዋጊ ድርጅቶች ብቅ እንዲሉ በማድረግ እና እንደ ኮርዶባዞ ያሉ በርካታ ቁጥር ያላቸው አመጽ ከተሞች እንዲታዩ ምክንያት ሆኗል ፡፡ ሮዛሪያዞ እና ቱኩማናዞ ፣ ሌሎችም አሉ ፡፡ የንዮን ዕጩነት ቢያግደውም ፣ በታዋቂው አመፅ በመነሳት አምባገነናዊ አገዛዙ በፖሮኒዝም ተሳትፎ የምርጫ መውጫ አደራጅ ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1973 ሶስተኛው ተብሎ የሚጠራውን የፕሬዚዳንትነት ምርጫ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫዎች ሕጋዊ ሆነ ፡፡ ፕሬዝዳንት ሄክተር ሆሴ ካማፖ ከለቀቁ በኋላ በዚያው ዓመት ጁዋን ዶንጎ ንዮን ለሶስተኛ ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ ፡፡ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እና ሚስቱ ማሪያ ኤቴላ ማርቲኔዝ ዴ ሮን ተተካ። ይህ ጊዜ በ 1973 በተከሰተው የነዳጅ ቀውስ እና በሰፊው የፖለቲካ አመፅ የተነሳ የአርጀንቲና ፀረ-ኮሙኒስት ህብረት (ሶስቴ ኤ) ተብሎ በሚጠራው የፖሊስ ኃይል ጥምረት የተነሳው ውስጣዊ ሁኔታ በተፋጠነ ሁኔታ ተለይቶ ይታወቃል። እ.ኤ.አ. ከ 1973 ጀምሮ ፖሊሶች እና ወታደራዊ ኃይሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎችን ገድለዋል - ብዙዎች “ታሳሪዎች ጠፍተዋል” - እንዲሁም እስረኞች በሚባሉ አዋጆች በተደነገገው የጭካኔ ማዕቀፍ ውስጥ የተጠረጠሩ የማቆያ ማዕከሎች መትከል ፡፡ እ.ኤ.አ. መጋቢት 24 ቀን 1976 በአገሮች ጥበቃ ስር በብሔራዊ ጥበቃ አማካኝነት በብሔራዊ መልሶ ማደራጀት ሂደት የሚጠራ አዲስ ዘላቂ አምባገነናዊ ስርዓት የሚሾም አዲስ የወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ተደረገ ፡፡ የተባበሩት በተመሳሳይ የዘር ማጥፋት ወንጀል በፍትህ በተገለፀው በሺዎች የሚቆጠሩ የጠፉ ሰዎች እና ማንነታቸው በመገደል የተጎዱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሕፃናትን በማጥፋት ፣ በማሠቃየት እና በተቃዋሚዎችን የማስወገድ ስርዓት ያለው እቅድ ተፈፃሚ ሆነ ፡፡ የመጀመሪያው የወታደራዊ ,ቴ ፣ ከግራ ወደ ቀኝ: - ኤሚሊ ማሳራ ፣ ር ይ ቪላ እና ኦርላንዶ አንጋስታ። በ 1985 በሰብአዊ መብት ላይ በተፈፀመ ወንጀል እስራት ተፈረደበት ፡፡ በምላሹም ‹የፕላዛ ዴ ማዮ እናቶች እና የፕላዛ ዴ ማዮ እናቶች አያቶች› ያሉ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች የተቋቋሙ ሲሆን ይህም በ ‹የጥፋተኞቹ የፍርድ እና የቅጣት ቅጣት› እና ማንነታቸው የተጎዱትን ሕፃናትን በማገገም ላይ ወሳኝ ሚና ይጫወታል ፡፡ ተሰር .ል። የሕብረቱ ንቅናቄ በጠቅላላው አጠቃላይ ጥቃቶችን ለማወጅ እስከሚታወቅ ድረስ ጠንካራ ተቃውሞ ተቋቁሟል ፣ የ መበታተን እና የሰራተኞች ማህበራት ጣልቃ ገብነት ፡፡ አምባገነኑ መንግስታት ዋና ዋና የንግድ ቡድኖችን በንቃት የሚደግፍ ፣ የመንግስት ቁልፍ ተግባሮችን የሚይዝ ፣ እንዲሁም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ዋና ዋና ሚዲያዎች ከታዋቂ ጋዜጠኞች እና ኮሚዩኒኬሽኖች ጋር ነበሩ ፡፡ የኢኮኖሚው ዕቅድ የቺካጎ ትምህርት ቤት መመሪያዎችን ተከትሏል - ብዙውን ጊዜ ከኒዮሊቤራሊዝም ጋር ተለይቷል ፡፡ የሕዝቡ አስፈላጊ ክፍል አምባገነንነቱን ደግ ል ፣ ሌላ ክፍል ደግሞ እንደ ያሉ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች መፈጠርን ወይም የሰራተኛ ማህበር እርምጃዎችን እና አድማዎችን በመቃወም ሌላ ዘርፍ ተቋቋመ ፡፡ እ.ኤ.አ. ከ 1983 ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ መንግስትን የሚያስተካክል የውጭ ዕዳ እ.ኤ.አ. በ 1976 ከ 7,700 ሚሊዮን ወደ 45,000 ሚሊዮን ደርሷልእ.ኤ.አ. በ 1983 ዶላር ፣ በብዙ ሁኔታዎች የኢኮኖሚ ቡድኖችን እና ሁለገብ ኩባንያዎችን ጥቅም ለማስጠበቅ የወንጀል ክዋኔዎች ውጤት ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1978 በጊል ቻናል አካባቢ ገደቦችን በመከተል በከባድ ቀውስ የተነሳ ሁለቱ አገሮችን ወደ ጦርነት አመጣ ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1982 ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር የፎልክላንድ ጦርነት እ.ኤ.አ. ለአርጀንቲና ሽንፈት ለወታደራዊው ስርዓት ውድቀት ካደረጓቸው ምክንያቶች መካከል አንዱና ለሚቀጥለው አመት አጠቃላይ ምርጫ ጥሪ እንዲቀርብ ጥሪ አቅርበዋል ፡፡ ዴሞክራሲ ማገገም እ.ኤ.አ. ከ 1983 እስከ 2003 ባለው ጊዜ የአርጀንቲና ታሪክ እ.ኤ.አ. አምባገነናዊው መንግሥት በነበረው የሰብአዊ መብት ጥሰት ወንጀል የተከሰሱ ሰዎች ክስ ተመስርቶበት የጀመረው የአርጀንቲና ታሪክ ምልክት ተደርጎ ነበር ፡፡ ሌሎች በደቡብ አሜሪካ የተገኙት - ዲሞክራሲያዊ የውጭ ዕዳ ቀውስ ፣ ግሎባላይዜሽን ጅምር ፣ ኒዮሊቤራል ተሐድሶዎች እና እ.ኤ.አ. በ 1998 የተጀመረው ከባድ የኢኮኖሚ ውድቀት እ.ኤ.አ. በ 2001 እና በደርዘን የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች ተገደሉ ፡፡ እ.ኤ.አ. በታህሳስ 20 ቀን 2001 እ.አ.አ. በአርጀንቲና ታሪክ ለሁለት አስርት ዓመታት በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚዘልቅ ሲሆን ዴሞክራሲያዊ ፕሬዝዳንቶች ለሌላ ዲሞክራሲያዊ መንገድ ለተመረጡ የፖለቲካ ፓርቲ ተተኪዎች ስልጣናቸውን በሚረከቡበት ጊዜ ነበር ፡፡ ዲሞክራሲያዊው መንግሥት ታህሳስ 10 ቀን 1983 እንደገና ተቋቋመ ፡፡ አዲሱ ፕሬዝዳንት ራዩል አልፈሰን የተባሉት የሪብሊክ ሲቪክ ህብረት ሰብአዊ መብት ጥሰትን ለመመርመር የወሰነ ሲሆን ይህም እንደገናም እንደገና አይ የሚል ርዕስ ያለው ነው ፡፡ የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወታደራዊ ቦርዶች ተፈርዶባቸው የተወሰኑት አባሎቻቸውም ተፈርዶባቸዋል ፣ ምንም እንኳን በእሱ ትእዛዝ እና በወታደራዊ ግፊት ቁጥጥር የተደረገ ቢሆንም ፡፡ በ 1984 በኬል ቻናል ላይ ከቺሊ ጋር የድንበር ክርክር አብቅቷል ፡፡ እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በ 1985 በአዲሱ የብራዚል ፕሬዝደንት ሆሴ ሳርኒ ከአዲሱ የዴሞክራሲያዊ ፕሬዝዳንት ሆሴ ሳርኒ ጋር በመተባበር በሺኮርጅር ስም የሚወጣውን የአካባቢ ውህደት ሂደት ለመጀመር እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. የ 1989 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ከተደረገ በኋላ በሃይመሪነት ሂደት የአገሪቱን የበላይነት ላይ ተጽዕኖ ያሳደረ ሲሆን አልፍሬንሰን ከፕሬዚዳንቱ ለመልቀቅ እና ከስድስት ወር በፊት ትዕዛዙን ለመቆጣጠር ተገደው የፍትህ አካላት ፓርቲ የሆኑት ካርሎስ ሜሜ ፡፡ በ 1989 በዋሽንግተን ስምምነት እና ከ ድጋፍ ጋር በሚስማማ መልኩ በሚኒስትር ዶንጊን ካቫሎ ጠንካራ የሥራ ድርሻ ላይ የዋጋ ግሽበትን አቆመ ፡፡ በማህበረሰቡ ውስጥ የጅምላ ሥራ አጥነት መጣ እና ወንጀል በከፍተኛ ሁኔታ ተባብሷል ፣ ሁለቱም በፖለቲካ አጀንዳ ላይ ማዕከላዊ ችግሮች ሆነዋል77 እ.ኤ.አ. በ 1991 አርጀንቲና በአሜሪካ ትእዛዝ መሠረት በብሔራዊ ኮንግረስ ፈቃድ ሳታደርግ ኢራን ላይ ጦርነት ገባች ፡፡78 እ.ኤ.አ. 1992 እ.ኤ.አ. በ 1994 ሁለት የእስራኤል የሽብር ጥቃቶች ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል ፡፡ በእስራኤል ኤምባሲ እና በኤኤምአይ ላይ የ 23 እና የ 85 ሰዎች ሞት በተፈጸመባቸው ወንጀለኞች ሳይገኙ ባለበት ሁኔታ በብዙ መሰናክሎች በመፈተሽ.799 ከ ቺሊ ጋር የድንበር ውዝግብ ተፈታ ፡፡ በሎጎ ዴል ዴርቶ ክልል ውስጥ ይገኛል ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1994 በአልሰንሰን እና በሜም መካከል የተደረገ ስምምነት ህገ-መንግስቱን እንዲሻሻል እና በሚቀጥለው ዓመት ሜም እንደገና ተሾመ ፡፡ ወደ ኢኳዶር እና ክሮሺያ የተደረገው የጦር መሳሪያ ዝውውር እንቅስቃሴ የሪዮ የጦር ፋብሪካን ፍንዳታ በመቃወም ፣ ከተማዋን እጅግ በመጎዳቱ ሰባት ሰዎችን ለህልፈት የዳረገው እና ​​ከፔሩ ጋር ያለውን ግንኙነት በከፍተኛ ሁኔታ ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል ፡፡ እና የፒክሴሮሮ እንቅስቃሴን ያስነሱ የመንገድ መሰናክሎች። እ.ኤ.አ. በ 1998 ለአራት ዓመታት የዘለቀ ውድቀት የጀመረው በአርጀንቲና ታሪክ ውስጥ እጅግ የከፋ ቀውስ አስከትሎ ነበር ፡፡ እ.ኤ.አ. በታህሳስ ወር 1999 የሕብረቱ አባል የነበረው የራሺያዊ ሲቪክ ህብረት ፈርናንዶ ዴ ላ ሩአ ፕሬዚዳንቱን ተረከበ። የሕዝቡን ጉድለትን ለመቀነስ እርምጃዎችን ወስ ል - የጡረታ ክፍያን ለመቀነስ እና የሠራተኛ መብቶችን ይበልጥ ተለዋዋጭ ለማድረግ ፣ አመላካችነት ተከትሎ ፡፡ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ቀውስ እየተባባሰ ሲመጣ ፣ መንግሥት ደግሞ የቀድሞውን የፕሬዚዳንት ሚንሜን ሚኒስትሩን ዶንጎ ካቫሎ ሾመ ፡፡ በጠቅላላ ማህበራዊ አመፅ ምክንያት የተከሰተ የባንክ ተቀማጭ ገንዘብ (“ኤል ኮራልቶ” በመባል የሚታወቅ መለኪያ) እንዲታገድ ትእዛዝ ሰጠ ፣ እ.ኤ.አ. በታህሳስ 20 ቀን 2001 ፕሬዝዳንታዊ ሥልጣኑን ለመልቀቅ አስችሏል ፡፡ በሁለት ቀናት እርግጠኛ አለመሆን ፣ አገሪቱ በውጭ ዕዳ ላይ ​​የተዘበራረቀችበትን ሁኔታ በመግለጽ ሀገሪቱ ወደ ነባሪነት የታወጀችበትን የአዶልፎ ሮድሪጊዛን አጭር መንግስት ጨምሮ በርካታ ፕሬዚዳንቶች ተተክለው ነበር ፡፡ እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 2 ቀን 2002 የሕግ መወሰኛው ምክር ቤት ኤድዋርዶ ዱሃዴሌን ከኦቲዮቲስታቲ ፓርቲ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት አድርጎ መረጠ ፡፡ ዱሃዴል “ኮሪልዮን. በዚህ ወቅት ድህነት ወደ የህዝብ ብዛት ወደ 56 ከመቶ አድጎ ደግሞ ወደ 26 በመቶ አድጓል ፡፡ ለሠራተኞች ላልሆኑ ሀላፊነቶች እቅዶች መመስረት እ.ኤ.አ. በግንቦት 2003 የሁለት ሚሊዮን እቅዶች ከፍተኛ ሆነ ፡፡ ወደ 135% የ ፣ የዛ ዓመት የዋጋ ግሽበት 41% ነበር እና የምግብ ዋጋ ጭማሪ ደግሞ 74.9% ደርሷል። ተፈጥሯዊ ክልሎች አርጀንቲና ብዙ የተለያዩ ክልሎች አሏት-እርጥብ ፓምፓ ፣ ደረቅ ፓምፓ - አንዳንድ ጊዜ የፓምፓስ ክልል ተብሎ የሚጠራ አንድ ነጠላ ክልል ፣ ሲሪያራስ ፓም ሙዝ ፣ ኩዮ ፣ የአርጀንቲና ሰሜን ምዕራብ ወይም ፣ የቻኮ ክልል ፣ መስጴጦሚያ ፣ ፓራጋኒያ እና አናታታዳ የአርጀንቲና ተፈጥሮአዊ ሀብት እጅግ ሰፊ ነው ፡፡ ከዓለም አቀፉ የተፈጥሮ ሀብት () አርጀንቲና እጅግ በጣም የቅርብ ጊዜ ዘገባ መሠረት እጅግ በጣም ሀብትና ተፈጥሮአዊ ብዝሃነት ያለው ዘጠነኛው ሀገር (ከ 150 በላይ ከሆኑት) ነው ፡፡ እ.ኤ.አ. ) በዓለም ላይ ካሉ ሰባት ተፈጥሮአዊ ድንቅ ነገሮች እንደ አንዱ ተቀደሱ ፡፡ የአርጀንቲና አህጉራዊ ክልል በአንዲስስ ፣ በደቡብ አትላንቲክ ውቅያኖስ እና በአንታርክቲክ አህጉር መካከል ይገኛል ፡፡ በአገሪቱ ውስጥ ሦስት ትላልቅ በግልፅ የተቀመጡ ጂዮግራፊያዊ ስፍራዎችን መለየት ይቻላል- መካከለኛው እና ሰሜናዊው ሜዳማ ሜዳዎች የደቡባዊው የፕላዝማስ ክልል ምዕራባዊው ተራራማ አካባቢ በሰሜናዊ የአገሪቱ ክፍል ጥቅጥቅ ያሉ እፅዋት ክልሎች ይገኛሉ ፡፡ በአንዳንድ ዘርፎች ጫካ ውስጥ ሲሆን በሌሎች ጫካዎች ደግሞ በቻኮ ክልል እና በ አይቤታ አካባቢዎች ይገኙበታል ፡፡ እነዚህ የበለፀጉ ዕፅዋት አካባቢዎች ከሌሎች የዘንባባ እርሻዎች እና ከሣር መሬቶች ጋር ይደባለቃሉ ፡፡ የሚስዮናዊያኑ ክልል ልዩ ነው ፣ የብራዚል የተራራ ሰንሰለቶች ማራዘሚያ ፣ ዝቅተኛ ግን ረዣዥም ተራራማ አካባቢዎች ፣ ዝቅተኛ እርጥበት ያለው እና ጫካ እፅዋት ፡፡ የአገሪቱ ሰሜናዊ ምዕራብ በጣም ከፍተኛ በሆነ ጠፍጣፋ ክልል ውስጥ ይገኛል ወይም በሀገሪቱ መሃል የፓምፓስ ሜዳ ይገኛል ፣ በሁለት ክልሎች ሊከፈል ይችላል-እርጥብ ፓምፓ እና ምዕራባዊ ወይም ደረቅ ፓምፓ። የኋለኛው ደግሞ የበለጠ አህጉራዊ የአየር ንብረት አለው ፡፡ እርጥበት ባለው ፓምፓ ውስጥ ሴራ ዴ ላ ቨንታና እና ታንዲሊያ (ከባህር ጠለል በላይ 500 ሜትር ከፍታ ካለው ከፍታ ጋር) 202 203 ብቸኛው የመሬት አቀማመጥ ሁኔታን የሚያፈርሱ እና የመሬት ውስጥ ፍሰት ናቸው በጣም ያረጀ የተራራ ክልል.202 የፓፓስ ሜዳ ለጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች እንዲሁም ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ ነው ፡፡ በሀገሪቱ መሃል-ምእራብ ምዕራብ ውስጥ በሳን ጁዋን ፣ ሚንዛዛ እና ሳን ሉዊስ ግዛቶች የተገነባው የኩዮ ክልል ነው ፣ አነስተኛ ተራራማ የሆነ እፎይታ ያለው ተራራዊ እፎይታ ይገኛል ፡፡ በደቡባዊ የሀገሪቱ ክፍል (የአርጀንቲና አንታርክቲካን ሳይቆጥር) ፓፓጋኒያን ነው ፣ ሰፊ የሆነ የፕላዝሃነስ እና ተራራማ አካባቢዎች የሪዮ ኔሮ ፣ የኑዊን ፣ ቹ ፣ የሳንታ ክሩዝ እና የዚራ ደሬ ፉዌጎ ግዛቶችን ያጠቃልላል። ፓራጋኒያ በሃይድሮካርቦኖች (ጋዝና ዘይት) የበለጸገ ፣ እንዲሁም የአርጀንቲና አህጉራዊ መደርደሪያዎች ፣ የአርጀንቲና ባሕረ ሰላጤ ፣ እንደ ሐይቅ ፣ ሳልሞን ፣ ወዘተ ባሉ ዝርያዎች የበለፀገ ነው። በግርጌዎች ውስጥ እንደ ዩራኒየም ፣ ብር ፣ ወዘተ ያሉ የተለያዩ ዝርያዎች የማዕድን ቁጠባዎች አሉ ፡፡ በጣም አስፈላጊ ወንዞች የሚገኙት በሰሜናዊ ምስራቅ እና በአገሪቱ ምስራቅ ምስራቅ ነው ፡፡ በምዕራባዊው ንፍቀ ክበብ ሶስተኛ ትልቁ ተፋሰስ ከሚገኘው የከዋንካ ዴልታ ፕላን ጋር ይዛመዳል ፡፡ የተጠቀሰው ተፋሰስ ዋና ዋና የፍሎረሰንት ኮርሶች የሚከተሉት ናቸው-ፓራጓይ ፣ ቤርሜሆ ፣ ፕሊሲሲ ፣ ሳላዶ (ዴ ኖት) ፣ ኡራጓይ እና ረዥሙ ፣ ፓራና። የመጨረሻዎቹ ሁለቱ አንድ ላይ በሪዮ ዴ ላ ፕላታ አከባቢ እስኪያገኙ ድረስ አብረው ይጓዛሉ ፡፡ ይህ አከባቢ በፕላኔቷ ላይ ትልቁ ሲሆን በአርጀንቲና ውቅያኖስ ወደሚገኘው የአትላንቲክ ውቅያኖስ ክፍል ይፈስሳል ፡፡ ሁለት አስፈላጊ ወንዞች ወደ ባሕሩ ይፈስሳሉ-ኮሎራዶ እና ኔሮ ወንዞች ፡፡ በሁለቱ ወንዞች መካከል ያለው መሬት መስጴጦሚያ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በሚርሴስ ፣ ኮርሬሴርስ እና ኢሬሬስ ግዛቶች ይጋራል ፡፡ አርጀንቲና በአሜሪካ ውስጥ 4989 ኪ.ሜ የውቅያኖስ ዳርቻዎች አሏት ፡፡ በአትላንቲክ ውቅያኖስ አህጉር በአህጉራዊ መደርደሪያው ላይ ባልተለመደ ሁኔታ ሰፊ እና አስፈላጊ የአሳ እና የሃይድሮካርቦን ሀብቶች ያሉት አርጀንቲና ባህር ተብሎ ይጠራል ፡፡ የባሕሩን መታጠቢያ የሚያጠፉት ባሕሮች በቆፍሮች እና ገደሎች መካከል ይለያያሉ። የቀዝቃዛው አንታርክቲክ እና ሞቅ ያለ የብራዚል ተለዋጭ መተካት የባሕሩ ሙቀት የሙቀት መጠን ከቀዝቃዛው ፍጥነት ጋር ተመሳሳይነት እንዳይቀንሰው ያስችላል ፣ ግን ልዩነቶች አሉት ፡፡ የደሴቲ ደቡባዊ የባህር ዳርቻ የባህር ዳርቻዎች የ ማለፊያ ሰሜን ዳርቻ ይመሰርታሉ። ግራን ቻኮ ክልል እንደ ሰሜናዊ እፀዋት እጽዋት በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ይገዛሉ ፡፡ የዛምበርግሊያ የዛፎች ዝርያ በጥሩ ሁኔታ የሚሰራጭ እና በአድባሩ ዛፍ እና በናባቾ ዛፍ ይወከላል ፡፡ ጥቁር እና ነጭ የካሮብ ዛፎች (ፕሮስ አልባባ እና ፕሮሶፒስ ) እንዲሁ ታዋቂ ናቸው ፡፡ ሳቫን በደረቅ አካባቢዎች ውስጥ ሲሆን በአንዲስስ አቅራቢያ ይገኛል ፡፡ የውሃ እፅዋት እፅዋት በክልሉ ለምርጥ በሆኑ እርጥበታማ አካባቢዎች ይበቅላሉ ፡፡ በሀገሪቱ ማዕከላዊ ክፍል ረግረጋማ ፓምፓ የተባለ ትልቅ ሜዳዋ ነው ፡፡ በመጀመሪያ ፓፓው ምንም ዛፍ አልነበረውም። ነገር ግን በሰዎች ጣልቃ ገብነት ምክንያት እንደ አሜሪካን ሲካሞር ወይም የባህር ዛፍ ያሉ አንዳንድ ከውጭ የሚመጡ ዝርያዎች ይገኛሉ ፡፡ በአካባቢው ከሚኖሩት የአገሬው ተወላጆች አንዱ ኦምቡ ፣ ሁልጊዜ አረንጓዴ ነው ፡፡ የፓምፓስ ሜዳዎች መሬቶች ከፍተኛ መጠን አላቸው። ይህም ክልሉ ለእርሻ እጅግ ፍሬያማ ያደርገዋል ፡፡ የምእራብ ምዕራብ ፓፓ ወይም ደረቅ ፓምፖ ከ 500 ሚ.ሜ / ዓመት በታች የዝናብ መጠን ይቀበላል ፣ እና ጠንካራ የሣር ወይም የእንጀራ እርሻ ነው። የእሱ ጣውላ በአብዛኛው በምዕራባዊው ፓምፓ ማዕከላዊ ክልል ከሚገኘው ኮማዌ ጋር ተመሳሳይ ነው ፣ እና “ኮዴን” ተብሎ በሚጠራው የበሰበሰ ዛፍ ደኖች ተሸፍነዋል ፡፡ እሱ ከርዮባባ እና ከሳን ሉዊስ አውራጃዎች ወደ ላ ላፓም እና ቡኤነስ አይሪስ ደቡባዊ ወሰኖች በሚሄድ ዲያግራናል ላይ ይሰራጫል። በአርጀንቲና ፓራጋኒያ ውስጥ አብዛኛዎቹ እፅዋት የተቆረቆረውን ደረቅ ሁኔታ ለመቋቋም በተለመዱ ቁጥቋጦዎችና እፅዋት የተሠሩ ናቸው። ሸለቆው ካልሆነ በስተቀር አፈሩ ጠንካራ እና ዐለት ነው እና ሰፋፊ እርሻን የማይቻል ያደርገዋል። በምዕራባዊ ፓራጋኒያ እና በቲሮራ ዴ ፉዌጎ ደሴት ላይ ጥሩ ደኖች ያድጋሉ። የክልሉ ተወላጅ የሆኑት ዝንቦች ፣ ፣ ፣ ፣ ፣ ማ ሴት እና አኩዋዋሪያ ሲሆኑ ፣ የአገሬው የብሮድባድ ዛፍ የተለያዩ የኖትፊግየስ ዝርያዎችን ጨምሮ ፣ ሎጋ እና ር. በደን ውስጥ ተክል ውስጥ የሚገኙት የውጭ ዛፎች ስፕሩስ ፣ ሳይፕረስ እና ጥድ ናቸው። የተለመዱ ዕፅዋቶች ኮፒሁ እና ኮላይሁ ናቸው። በኩዮ ውስጥ በከፊል ደረቅ-እሾህ ቁጥቋጦ ቁጥቋጦዎች እና ሌሎች የካሮፊቲክ እፅዋት በብዛት ይገኛሉ። በተለያዩ ዘይቶች ሁሉ ፣ የወንዝ ሳርዎችና ዛፎች ጉልህ በሆነ ቁጥር ያድጋሉ ፡፡ አካባቢው ለትላልቅ የወይን ተክል እድገት ዕድገት ምቹ ሁኔታዎችን ያቀርባል ፡፡ በሰሜን ምዕራብ አርጀንቲና ውስጥ በርካታ የከብት ዝርያዎች አሉ ፡፡ በከፍተኛ ከፍታ ላይ (ከ 4000 ማይል / በላይ) ፣ በከፍታው ከፍታ ምክንያት ምንም ዋና እፅዋት አያድጉም ፣ እናም አፈሩ ከማንኛውም የዕፅዋት ህይወት እጦት የለውም ፡፡ አብዛኛው አርጀንቲና የሚገኘው በ ግራፊያዊ ክልል (ካሬራ ፣ 1976) ሲሆን በዚህ ክልል ውስጥ 4 ጎራዎች ይወከላሉ ፡፡ የአርጀንቲና ትልቁ የአበባ እፅዋት ሀብታም በሰሜናዊ የአገሪቱ ክፍል በሚገኙት የአማዞን ደን ደኖች ውስጥ ይገኛሉ ፡፡ የቼክኖ ጎራ በበኩሉ እጅግ በጣም ሰፊ ምስጥር ነው ፣ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ እስከ አንዲያን አካባቢ ድረስ ባሉት ቋጥኞች እና ሳቫናዎች እንዲሁም ከቦሊቪያ እና ፓራጓይ እስከ ሰሜን እስከ ቹውት አውራጃ ባለው ድንበር ይገኝበታል ፡፡ ለአርጀንቲና ደቡባዊ እና ምዕራብ የአኔስ ፓትራጋኒያን ጎራ ነው ፣ ይህም የአንዲስስ ከፍታ ከፍታ ያላቸውን መናፈሻዎች ፣ የፓና እና የፓትጎሪያን ባሕረ ሰላጤዎችን ፣ እና ንዑስ-አንታርክቲካ ጎራዎችን በመያዝ እና ፓትጎኒያን አንዲስ. የአርጀንቲና ክልል እንደ ኬክሮስ ፣ ከፍታ ፣ የአፈር ሁኔታ ፣ ወዘተ ባሉ የተለያዩ ሁኔታዎች ምክንያት በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ በርካታ የአዮሚኖች እና ባዮቶፖቶችን ያካትታል። ይህ ዓይነቱ ልዩነት በራስ-ሰርቶኒየስ ፋና ውስጥ ትልቅ ልዩነቶች አሉት ፡፡ የእንስሳትን ዝርያ መኖር ለመገንዘብ የእያንዳንዱ ሥነ ምህዳራዊ አውታረመረብ ምን እንደ ሆነ እና በውስጡም እንደ እያንዳንዱ ባዮቴፔ ምን እንደሚመስል ለመረዳት አስፈላጊ ነው ፣ ነገር ግን አርጀንቲና በሚባልበት ሁኔታ በዝርዝር የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳራዊ ልዩነት ምክንያት በዝርዝር መግለፅ አይቻልም ማለት ይቻላል። አብዛኛዎቹ የአርጀንቲና አጥቢ እንስሳቶች ከሰሜን አሜሪካ በሺዎች ከሚቆጠሩ ዓመታት በፊት የመጡ ናቸው ፡፡ ከቀዳሚው የጎንዋና ሜጋ እስከ ዛሬ ድረስ በሕይወት የተረፉት ጥቂቶች ናቸው ፡፡ ከኋለኞቹ መካከል በጣም ታዋቂ የሆኑት አርማሞሎስ ፣ ውሃዎች ፣ እና እንደ ኦፖምስ ፣ የጫካው ትንሽ ዝንጀሮ ወይም የቀይ አረም እና የዱር እንስሳት (ሁሉም ድንቢጦች) ናቸው ፡፡ በዚህ መንገድ ፣ የአርጀንቲና ግዛቱ (እንደ መላው የደቡብ ኮይን ተመሳሳይ ነው) የሚመሰረተው የፊውዳጃ አካል እና የኒውኦሮፖሎጂ ምህዳሩ ነው ፣ የአብዛኛው ክልል የአየር ሁኔታ እና ቅዝቃዛ የአየር ንብረት ቅኝቶችን እና የግንኙነት እድገቶችን ያስገኛል እንዲሁም ፈጣን ማበረታቻዎችን ፈቅደዋል ከ 9 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በታላቁ አሜሪካን ልውውጥ ምክንያት ከነበረው የሂሎቲክ ክልል የመጡ ዝርያዎች ወይም ግማሽ ሚሊኒየም ያመረቱ እና እስከ አሁን ድረስ። ብዛት ያላቸው የእንስሳት ዝርያዎች የሚገኙት በሐሩር ክልል እና በተለይም በደቡብ ሰሜናዊ ክፍል ነው ፡፡ እንደ ያጊዋሬቴ ፣ ማ እና ኦዚል ያሉ ትልልቅ ድመቶች አሉ ፡፡ እንደ ወይም ተኩላ ያሉ ታላላቅ መርጃዎች ፣ እንደ ድብ ድብ የሚባሉት የበርገር ዝርያዎች ፣ እንደ አንበጣ ጦጣ) እንደ ሁለት ተጓዳኝ ዝርያዎች ሁሉ ትልቅ ባሕረኞች ፡፡ ሌሎች እንስሳት ደግሞ ታፓር ፣ ካፒቢባስ ፣ ሁለት የውቅያኖስ ዝርያዎች ፣ ታላቁ ታላቁ ፣ ሦስት የከብት ዝርያዎች ፣ ግዙፍ ኦተር ፣ ኮቲ እና በርካታ የባህር ኤሊ ዝርያዎች ናቸው ፡፡ በአርጀንቲና ድንበር ተሻጋሪ ክልል እንደ ሃርፒ ንስር (በአህጉሪቱ ላይ ትልቁ አዳኝ ወፍ) ፣ በደርዘን የሚቆጠሩ ትናንሽ የ ዝርያዎች ፣ ሶስት የፍሬዎዶስ ዝርያዎች ፣ አምስት ቱቱካኖች እና የተለያዩ የፓሮዎች ዝርያዎች ያሉ ብዙ ወፎች አሉ ፡፡ ማዕከላዊው ጸሎቶች በታይቱስ ፣ በቀለማት ያሸበረቁት እና በታይማን ወይም በደቡብ አሜሪካ ሰጎን ተሞልተዋል ፡፡ የተለያዩ አርኬቶች ፣ ዳክዬዎች እና ፍርስራሽዎች እንዲሁም በርካታ የአጋዘን እና ቀበሮዎች ዝርያዎችም እንዲሁ ይኖራሉ ፡፡ አንዳንድ ዝርያዎች ወደ ፓራጋኒያ ይዘራሉ። የምእራባዊ ተራራዎች የተለያዩ እንስሳት መኖሪያ ናቸው ፡፡ ከነዚህም መካከል በደቡብ አሜሪካ ውስጥ በጣም የሚታወቁ ዝርያዎች የሆኑት ላላላ ፣ ታሩካ ፣ ጓዋንኮ እና ቫይኪን ናቸው ፡፡ በተጨማሪም በዚህ ክልል ውስጥ የአንዲያን ድመት እና ኮንዶር ናቸው ፡፡ የኋለኛው በዓለም ላይ ትልቁ የበረራ ወፍ እንዲሁም ወደ ከፍተኛ ከፍታ ከሚወጡት መካከል አንዱ ነው። ም ፣ ሑሙል ፣ ዱ (በዓለም ላይ ትንሹ አጋዘን) እና አስተዋውቀው የነበረው የዱር ዋልታ በደቡብ አርጀንቲና ይኖራል። የፓራጎኒያ የባሕር ዳርቻ በእንስሳት ሕይወት ውስጥ የበለፀገ ነው-የዝሆን ማኅተም ፣ የባህሩ አንበሳ ፣ የባህር አንበሳ እና የተለያዩ የፔንግዊን ዝርያዎች። በደቡባዊው መጨረሻ ዓሦችን የሚመገቡት ኮርማዎች ናቸው ፡፡ የአርጀንቲና የመሬት ዳርቻዎች የውሃ ብዛት አላቸው ፡፡ እንደ ዶልፊኖች እና ዓሣ ነባሪዎች ያሉ አጥቢ እንስሳት አሉ ፡፡ በጣም አስደናቂ ከሆኑት ዓሳ ነባሪዎች አንዱ ትክክለኛው ዓሳ ነባሪ ነው ፣ ከነ ገዳይ ነባሪዎች ጋር የ ላዴስ ባሕረ ገብ መሬት እና የፖርቶ ማሪያን የቱሪስት መስህብ ናቸው። የባህር ውስጥ ዓሳ ሳርዲን ፣ ሀክ ፣ ሳልሞን እና የውሻ ዓሳ ያጠቃልላል ፡፡ ስኩዊድ እና የሸረሪት ክሬም እንዲሁ በቲራራ ዴ ፉዌጎ ውስጥ ይገኛሉ ፡፡ በአርጀንቲና የሚገኙት ወንዞች እና ጅረቶች እንደ ትሩፋት ያሉ እንደ ትሬንት ያሉ እና የደቡብ አሜሪካ ዓሳ ዓሦች ብዙ ዝርያዎች አሉት ፡፡ አርጀንቲና እና የደቡብ አሜሪካ ንዑስ ንዑስ ንጥረ ነገር በብዝበዛ እና ያልተለመዱ የአቪፊና ዝርያዎች ተለይተው ይታወቃሉ ፣ በአህጉራዊ አሜሪካዊ አርጀንቲና ውስጥ በሁሉም ዓይነቶች 1400 የአእዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ ፣ ምንም እንኳን በጥቂቶች ጥቂቶች ብቻ ቢሆኑም ብዙዎች ግን ጎልቶ ወጥቷል (በሰው ልጆች ምክንያት) የመጥፋት አደጋ አነስተኛ ነው በዚህ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ በአገሪቱ ውስጥ ወደ 400 የሚጠጉ የእንስሳት ዝርያዎች አሉ (እ.ኤ.አ. በ 2019 ከአስር ዓመት ገደማ ጥናት በኋላ 15 አዳዲስ የአርጀንቲና አጥቢ እንስሳት ተገኝተዋል) ከአንድ ሩብ በላይ 239 ዝርያዎች) የመጥፋት አደጋ ላይ ናቸው ፣ ሁሉም ማለት ይቻላል ከሰው ልጅ ምክንያቶች። በአርጀንቲና ውስጥ የሚኖሩት የኦፊድያ ዝርያዎች ቡኒ ገንቢውን ፣ መርዛማውን ባራራ እና ራታን ያካትታሉ። የአርጀንቲና ባህል በብዙ ብሔረሰቦችና ባህላዊ ባሕሎች ፣ በሕዝቦ እና በሌሎች ባህሎች ባሕል ፣ በባህላዊ አገላለ ች ጠንካራ ትስስር እና መሻሻል እና ዘመናዊነት በብዙ ጎሳዎች መታወቅ እና ስሜት የአውሮፓ እና የላቲን አሜሪካ ባህሎች ፣ የተወሰኑ የእስያ እና የአፍሪካ መዋጮዎች ነበሩ። የአርጀንቲና ባህል በስደቱ ዓመታት የተገኙት የሌሎች ድብልቅ መነሻ ነው። ርዕዮተ ዓለም ፣ ማህበራዊ-ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰባቸው እና ቋንቋቸው ፣ የነፃነታቸው እምነት ፣ ዴሞክራሲ እና ለሰብአዊ መብት መከበር ጎልቶ ይታያል ፡፡ በአገሪቱ ውስጥ የተለያዩ ባህላዊ እንቅስቃሴዎች እና አስፈላጊ የስነጥበብ እንቅስቃሴ ፣ በቲያትር ፣ በሥዕል ፣ በሥዕል ፣ በሙዚቃ እና በሥነ-ጽሑፍ ውስጥ ትልቅ የስነ-ጥበባት እንቅስቃሴ አለ ፡፡ ኮንፈረንሶች ፣ ኮንሰርቶች ፣ ኤግዚቢሽኖች ፣ ቤተ መዘክርዎች ፣ ኮርሶች ፣ ቲያትር እና የባሌ ዳንስ ትርኢቶች በየቀኑ በአገሪቱ ውስጥ በጣም አስፈላጊ ከተሞች እና በዋናነት በቡኖ አይሪስ ውስጥ ይሰጣሉ ፡፡ በሁሉም ትላልቅ ከተሞች ውስጥ ሲኒማቶግራፊ እና የትያትር ቤቶች ትርቶች በብዛት ይገኛሉ ፡፡ እንደ ታንጎ ፣ አፈ ታሪክ (ቀደም ሲል ታንጎ በቡኤነስ አይሪስ እና ሮዛሪየስ ከተሞች ውስጥ ያሉ ታዋቂ ሙዚየሞች ነበሩ) ፣ ነገር ግን ከ “ጋሊያ ቪያጃ” እና ከ መጀመሪያ ጋር ፣ የፓስካል ኮንትራክተርስ እና ካርሎስ ዘፈን ቆሙ ፡፡ ከሌሎች ሙዚቀኞች ጋር እንደ አንዱ የተለመደ የአርጀንቲና ሙዚቃ ሙዚቃ አንዱ እንደመሆኑ በዓለም ዙሪያ የሚታወቅ ቢሆንም የአርጀንቲና ተረት ተረት ጠንካራ በመሆን የአርጀንቲና አፈ ታሪክ በጥብቅ ይሳተፉ ፡፡ የአርጀንቲና ባህላዊ ሙዚቃ) እና የአርጀንቲና ብሔራዊ ዓለት (በ 1960 እና 1980 መካከል “ተራማጅ ሙዚቃ” እና “ኒው አርጀንቲና የከተማ ሙዚቃ” የሚታወቅ) በልዩ ዝግጅቶች እና በጅምላ በተገኙባቸው ቦታዎች ይጨፈራሉ ፡፡
18414
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%AD%E1%88%96%E1%8B%8B%20%E1%88%9D%E1%88%B5%E1%8A%AD%E1%88%AE%E1%89%BD
የይሖዋ ምስክሮች
የይሖዋ ምሥክሮች ሉዓላዊው ጌታ አንድ እርሱም ይሖዋ ነው ብለው የሚያምኑ ክርስቲያናዊ ሃይማኖት ነው። የይሖዋ ምሥክሮች ዘመናዊ እንቅስቃሴ የጀመሩት በ1870ዎቹ ዓመታት ነው። በመጀመሪያ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ተብለው ይጠሩ ነበር። በ1931 ግን የይሖዋ ምሥክሮች የሚለውን ቅዱስ ጽሑፋዊ ስም ተቀበሉ። (ኢሳይያስ 43፡10) አብዛኞቹ የይሖዋ ምሥክሮች ጉባኤዎች በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ ይሰበሰባሉ። አብዛኞቹ ስብሰባዎች በይሖዋ ምስክሮች የስብሰባ አዳራሾች ውስጥ ይካሄዳሉ። በተጨማሪም የይሖዋ ምሥክሮች በየዓመቱ ሦስት ትላልቅ ስብሰባዎች ያካሂዳሉ። የይሖዋ ምሥክሮች ዋና መሥሪያ ቤት የሚገኘው በኒው ዮርክ ነው።። የይሖዋ ምሥክሮችን ከሌሎች ሃይማኖቶች የተለዩ የሚያደርጓቸው እምነቶች ምንድን ናቸው? መጽሐፍ ቅዱስ:- የይሖዋ ምሥክሮች ጠቅላላው መጽሐፍ ቅዱስ በአምላክ መንፈስ አነሣሽነት የተጻፈ የአምላክ ቃል ነው ብለው ያምናሉ፤ በሰው ወግ ላይ የተመሠረተን እምነት ከመከተል ይልቅ ለእምነቶቻቸው ሁሉ መመዘኛ የሚያደርጉት መጽሐፍ ቅዱስን ነው። አምላክ:- ይሖዋ ብቻ እውነተኛ አምላክ መሆኑን በማመን ያመልኩታል። ስለ እርሱና እርሱ ለሰው ልጆች ስላወጣቸው ፍቅራዊ ዓላማዎች ለሌሎች ሰዎች በግልጽ ይናገራሉ። ስለ ይሖዋ አምላክ ለሕዝብ የሚመሰክር ማንኛውም ሰው የአንድ ቡድን ይኸውም “የይሖዋ ምሥክሮች” አባል መሆኑ ይታወቃል። ኢየሱስ ክርስቶስ:- የይሖዋ ምሥክሮች ኢየሱስ ክርስቶስ አንደኛው የሥላሴ አካል ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱስን እንደሚያንብቡት የአምላክ ልጅ፣ የአምላክ ፍጥረታት በኩር፤ ሰው ከመሆኑ በፊት ሕልውና የነበረው፤ ሕይወቱ ከሰማይ ወደ ድንግል ማርያም ማኅፀን የተዛወረ፤ መሥዋዕት የሆነው ፍጹም ሰብዓዊ ሕይወቱ ለሚያምኑበት ሁሉ የዘላለም ሕይወት መዳን የሚያስገኝ እንደሆነና ከ1914 እ.ኤ.አ. ጀምሮ አምላክ በምድር ሁሉ ላይ በሰጠው ሥልጣን ንጉሥ ሆኖ እየገዛ እንዳለ ያምናሉ። የአምላክ መንግሥት:- የይሖዋ ምሥክሮች የሰው ልጆች ተስፋ የአምላክ መንግሥት ብቻ ናት ብለው ያምናሉ። ይህች መንግሥት እውን መስተዳድር ነች፤ ሁሉንም ሰብዓዊ መስተዳድሮች ጨምሮ የአሁኑን ክፉ የነገሮች ሥርዓት በቅርቡ በማጥፋት ጽድቅ የሚኖርባትን አዲስ ሥርዓት ታቋቁማለች። ሰማያዊ ሕይወት:- 144,000 በመንፈስ የተቀቡ ክርስቲያኖች ከክርስቶስ ጋር በሰማያዊ መንግሥቱ ተካፋዮች በመሆን አብረውት ነገሥታት ሆነው እንደሚገዙ ያምናሉ። “ጥሩ” የሆኑ ሰዎች በሙሉ የሚያገኙት ሽልማት ወደ ሰማይ መሄድ ነው ብለው አያምኑም። ምድር:- አምላክ ለምድር ያለው የመጀመሪያ ዓላማ እንደሚፈጸም፣ ምድር ይሖዋን በሚያመልኩ ሰዎች ከዳር እስከ ዳር እንደምትሞላ፣ እነዚህም ሰዎች ሰብዓዊ ፍጽምና አግኝተው ለዘላለም እየተደሰቱ መኖር እንደሚችሉ፣ ሙታንም እንኳ ሳይቀሩ ከእነዚህ በረከቶች ተካፋዮች ለመሆን ከሞት እንደሚነሡ ያምናሉ። ሞት:- ሙታን ፈጽሞ አንዳች ነገር እንደማያውቁ፤ በአንድ ዓይነት መንፈሳዊ ዓለም ውስጥ በሥቃይ ወይም በደስታ ላይ እንዳልሆኑ፣ በአምላክ አእምሮ ውስጥ ከመታሰባቸው በቀር በሌላ መንገድ በሕይወት እንደሌሉ፤ በዚህም ምክንያት ወደ ፊት የሚኖራቸው ተስፋ የተመካው በትንሣኤ ላይ እንደሆነ ያምናሉ። የመጨረሻ ቀኖች:- ከ1914 ጀምሮ የምንኖረው በዚህ ክፉ የነገሮች ሥርዓት የመጨረሻ ቀኖች ውስጥ እንደሆነ፣ በ1914 የተፈጸሙትን ነገሮች የተመለከቱ አንዳንድ ሰዎች የአሁኑ ክፉ ዓለም ሲጠፋ እንደሚያዩ፣ ጽድቅ ወዳድ የሆኑት ግን ከጥፋቱ ተርፈው በጸዳች ምድር ላይ እንደሚኖሩ ያምናሉ። ከዓለም የተለዩ መሆን:- ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ተከታዮቹ ሲናገር “ከዓለም አይደሉም” እንዳለው የይሖዋ ምሥክሮችም የዚህ ዓለም ክፍል ላለመሆን ከልብ ይጥራሉ። ለሰው እውነተኛ ክርስቲያናዊ ፍቅር ያሳያሉ። በፖለቲካዊ ጉዳዮች አይሳተፉም ወይም በማንኛውም ብሔር ውስጥ በሚደረጉ ጦርነቶች ጣልቃ አይገቡም። ለቤተሰቦቻቸው የሚያስፈልጉትን ቁሳዊ ነገሮች ማቅረብ ቢኖርባቸውም ዓለም በጉጉት የሚያሳድዳቸውን ቁሳዊ ሀብቶች ማሳደድ፣ የግል ዝና ማግኘትና ከመጠን በላይ በተድላ መጠመድ አይፈልጉም። የመጽሐፍ ቅዱስን ምክር ተግባራዊ ማድረግ:- በቤት ውስጥ፣ በትምህርት ቤት፣ በሥራ ቦታና በጉባኤያቸው በየዕለቱ የአምላክን ቃል በሥራ ላይ ማዋል አስፈላጊ እንደሆነ ያምናሉ። አንድ ሰው ባለፈው ጊዜ ይከተለው የነበረው አኗኗር ምንም ይሁን ምን የአምላክ ቃል የሚያወግዛቸውን ሥራዎች ከተወና አምላካዊ ምክርን በሥራ ላይ ካዋለ ከይሖዋ ምሥክሮች አንዱ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን የይሖዋ ምሥክር ከሆነ በኋላ ማንም ሰው ምንዝር፣ ዝሙት፣ ግብረ ሰዶም እየፈጸመ፣ አደንዛዥ ዕፅ እየወሰደ፣ እየሰከረ፣ እየዋሸ ወይም እየሰረቀ እኖራለሁ ቢል ከድርጅቱ ይወገዳል። የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ ? (በራሳቸው አንደበት) አምላክ። እውነተኛና ሁሉን ቻይ የሆነውን ይሖዋ የተባለውን አንድ አምላክ እናመልካለን። (መዝሙር 83:18፤ ራእይ 4:11) ይሖዋ የአብርሃም፣ የሙሴ እና የኢየሱስ አምላክ ነው።—ዘፀአት 3:6፤ 32:11፤ ዮሐንስ 20:17 መጽሐፍ ቅዱስ። መጽሐፍ ቅዱስ አምላክ ለሰው ልጆች በመንፈሱ አማካኝነት ያስጻፈው መልእክት እንደሆነ እናምናለን። (ዮሐንስ 17:17፤ 2 ጢሞቴዎስ 3:16) እምነታችን የተመሠረተው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በሆኑት በ66ቱም መጻሕፍት ላይ ነው፤ እነዚህ መጻሕፍት በተለምዶ “ብሉይ ኪዳን” እና “አዲስ ኪዳን” በመባል ይታወቃሉ። ፕሮፌሰር ጄሰን ቤዱን የይሖዋ ምሥክሮች “የሚያምኑበትም ሆነ የሚያደርጉት ነገር ሙሉ በሙሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ያደርጋሉ እንጂ አንድን ነገር አስቀድመው ከወሰኑ በኋላ ያንን የሚደግፍ ሐሳብ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለማግኘት አይሞክሩም” በማለት ጽፈዋል። ሙሉውን መጽሐፍ ቅዱስ እንቀበላለን፤ ሆኖም ሁሉም ነገር ቃል በቃል መወሰድ አለበት የሚል እምነት የለንም። የተወሰኑት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የተጻፉት በዘይቤያዊ ወይም በምሳሌያዊ አነጋገር ስለሆነ ቃል በቃል መወሰድ እንደሌለባቸው እንገነዘባለን። ኢየሱስ። የኢየሱስን ትምህርትም ሆነ እሱ የተወውን ምሳሌ እንከተላለን፤ በተጨማሪም የአምላክ ልጅ እንዲሁም አዳኝ እንደሆነ በማመን እናከብረዋለን። (ማቴዎስ 20:28፤ የሐዋርያት ሥራ 5:31) በመሆኑም ክርስቲያን ተብለን እንጠራለን። (የሐዋርያት ሥራ 11:26) እንዲሁም ኢየሱስ ሁሉን ቻይ አምላክ እንዳልሆነና ለሥላሴ ትምህርት መሠረት የሚሆን ቅዱስ ጽሑፋዊ ማስረጃ እንደሌለ ከመጽሐፍ ቅዱስ አውቀናል።—ዮሐንስ 14:28 የአምላክ መንግሥት። የአምላክ መንግሥት እውን የሆነ መስተዳድር እንጂ በክርስቲያኖች ልብ ውስጥ ያለ ነገር አይደለም። ይህ መንግሥት ሰብዓዊ መንግሥታትን የሚተካ ሲሆን አምላክ ለምድር ያለው ዓላማ እንዲፈጸም ያደርጋል። (ዳንኤል 2:44፤ ማቴዎስ 6:9, 10) የአምላክ መንግሥት እነዚህን እርምጃዎች የሚወስደው በቅርቡ ነው፤ ምክንያቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች እንደሚጠቁሙት የምንኖረው “በመጨረሻዎቹ ቀናት” ውስጥ ነው።—2 ጢሞቴዎስ 3:1-5፤ ማቴዎስ 24:3-14 ኢየሱስ በሰማይ ያለው የአምላክ መንግሥት ንጉሥ ነው። መግዛት የጀመረው በ1914 ነው።—ራእይ 11:15 መዳን። ሰዎች ከኃጢአትና ከሞት መዳን የሚችሉት በኢየሱስ ቤዛዊ መሥዋዕት አማካኝነት ነው። (ማቴዎስ 20:28፤ የሐዋርያት ሥራ 4:12) አንድ ሰው ከዚህ መሥዋዕት ጥቅም ማግኘት ከፈለገ በኢየሱስ ማመን ብቻ ሳይሆን አኗኗሩን መለወጥና መጠመቅ ይኖርበታል። (ማቴዎስ 28:19, 20፤ ዮሐንስ 3:16፤ የሐዋርያት ሥራ 3:19, 20) አንድ ሰው የሚያደርገው ነገር እምነቱ ሕያው መሆን አለመሆኑን ያሳያል። (ያዕቆብ 2:24, 26) ይሁንና መዳን በሥራ ሳይሆን ‘በአምላክ ጸጋ’ የሚገኝ ነገር ነው።—ገላትያ 2:16, 21 ሰማይ። ይሖዋ አምላክ፣ ኢየሱስ ክርስቶስና ታማኝ መላእክቱ የሚኖሩት በመንፈሳዊው ዓለም ማለትም በሰማይ ነው። * (መዝሙር 103:19-21፤ የሐዋርያት ሥራ 7:55) በአንጻራዊ ሁኔታ ሲታይ ጥቂት ቁጥር ያላቸው ማለትም 144,000 ሰዎች ከሞት ተነስተው በሰማይ ከኢየሱስ ጋር ይገዛሉ።—ዳንኤል 7:27፤ 2 ጢሞቴዎስ 2:12፤ ራእይ 5:9, 10፤ 14:1, 3 ምድር። አምላክ ምድርን የፈጠረው ለሰው ልጆች መኖሪያ እንድትሆን ነው። (መዝሙር 104:5፤ 115:16፤ መክብብ 1:4) አምላክ ታዛዥ የሆኑ የሰው ልጆችን ገነት በምትሆነው ምድር ላይ ፍጹም ጤናና የዘላለም ሕይወት በመስጠት ይባርካቸዋል።—መዝሙር 37:11, 34 ክፋትና መከራ። ክፋትና መከራ የጀመሩት ከአምላክ መላእክት አንዱ በማመፁ ነው። (ዮሐንስ 8:44) ይህ መልአክ ካመፀ በኋላ “ሰይጣን” እና “ዲያብሎስ” ተብሎ መጠራት የጀመረ ሲሆን የመጀመሪያዎቹ ሰብዓዊ ባልና ሚስት በዓመፅ ድርጊቱ እንዲተባበሩት አሳምኗቸዋል፤ ይህ ደግሞ በዘሮቻቸው ላይ አስከፊ መዘዝ አስከትሏል። (ዘፍጥረት 3:1-6፤ ሮም 5:12) ሰይጣን ላነሳው አከራካሪ ጉዳይ መልስ ለመስጠት አምላክ በምድር ላይ ክፋትና መከራ እንዲኖር ፈቅዷል፤ ሆኖም እነዚህ ነገሮች ለዘላለም እንዲቀጥሉ አይፈቅድም። ሞት። ሰዎች ሲሞቱ ከሕልውና ውጪ ይሆናሉ። (መዝሙር 146:4፤ መክብብ 9:5, 10) በእሳታማ ሲኦል አይሠቃዩም። አምላክ በትንሣኤ አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ከሞት እንዲነሱ ያደርጋል። (የሐዋርያት ሥራ 24:15) ይሁንና ከሞት ከተነሱ በኋላ የአምላክን መንገድ ለመከተል ፈቃደኛ ያልሆኑ ሰዎች ለዘላለም ይጠፋሉ፤ የትንሣኤ ተስፋም አይኖራቸውም።—ራእይ 20:14, 15 ቤተሰብ። አምላክ የጋብቻ ዝግጅትን ያስጀመረው አንድን ወንድና ሴት በማጣመር ሲሆን እኛም ይህን በጥብቅ እንከተላለን፤ ለፍቺ ምክንያት የሚሆነው የፆታ ብልግና ብቻ እንደሆነ እናምናለን። (ማቴዎስ 19:4-9) በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚገኙት ጥበብ ያዘሉ ምክሮች የቤተሰብ ሕይወት ስኬታማ እንዲሆን እንደሚረዱ እናምናለን።—ኤፌሶን 5:22 እስከ 6:1 አምልኳቸው። መስቀልን ወይም ሌሎች ምስሎችን ለአምልኮ አይጠቀሙም። (ዘዳግም 4:15-19፤ 1 ዮሐንስ 5:21) በአምልኳቸው ውስጥ ትልቅ ቦታ ከሚሰጧቸው ነገሮች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦ ለአምላክ መጸለይ።—ፊልጵስዩስ 4:6 መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብና ማጥናት።—መዝሙር 1:1-3 ከመጽሐፍ ቅዱስ በተማርነው ነገር ላይ ማሰላሰል።—መዝሙር 77:12 ለጸሎት፣ መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥናት፣ ለመዘመር፣ እምነታችንን ለመግለጽና የእምነት ባልንጀሮቻችንንም ሆነ ሌሎችን ለማበረታታት መሰብሰብ።—ቆላስይስ 3:16፤ ዕብራውያን 10:23-25 ‘የመንግሥቱን ምሥራች’ መስበክ።—ማቴዎስ 24:14 ችግር ላይ የወደቁትን መርዳት።—ያዕቆብ 2:14-17 የመንግሥት አዳራሾችን እንዲሁም ዓለም አቀፉን የስብከት ሥራ ለማስፋፋት የሚያገለግሉ ሌሎች ሕንጻዎችን መገንባትና መጠገን።—መዝሙር 127:1 በተፈጥሮ አደጋ የተጎዱ ሰዎችን መርዳት።—የሐዋርያት ሥራ 11:27-30 ድርጅታችን። በጉባኤዎች የተደራጀን ሲሆን እያንዳንዱን ጉባኤ በበላይነት የሚከታተለው የሽማግሌዎች አካል ነው። ሆኖም ሽማግሌዎች የቀሳውስት ቡድን አይደሉም፤ እንዲሁም ደሞዝ አይከፈላቸውም። (ማቴዎስ 10:8፤ 23:8) አስራት አንጠይቅም፤ በስብሰባዎቻችን ላይም ገንዘብ አይሰበሰብም። (2 ቆሮንቶስ 9:7) ለምናደርጋቸው ሥራዎች የገንዘብ ድጋፍ የምናገኘው ስማቸው የማይገለጽ ለጋሾች ከሚያደርጉት መዋጮ ነው። በዋናው መሥሪያ ቤት የሚያገለግለው የበላይ አካል በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ የይሖዋ ምሥክሮች አመራር ይሰጣል፤ የበላይ አካሉ አባላት ጥቂት ቁጥር ያላቸው የጎለመሱ ክርስቲያኖች ናቸው።—ማቴዎስ 24:45 አንድነታችን። እምነታችን በዓለም አቀፍ ደረጃ አንድ አድርጎናል። (1 ቆሮንቶስ 1:10) በተጨማሪም በመካከላችን በኑሮ ደረጃ፣ በጎሣ፣ በዘር ወይም በመደብ ክፍፍል እንዳይኖር ጥረት እናደርጋለን። (የሐዋርያት ሥራ 10:34, 35፤ ያዕቆብ 2:4) አንድነት አለን ሲባል የግል ምርጫና አመለካከት የለንም ማለት አይደለም። እያንዳንዱ የይሖዋ ምሥክር በመጽሐፍ ቅዱስ በሠለጠነ ሕሊናው ተጠቅሞ የራሱን ውሳኔ ያደርጋል።—ሮም 14:1-4፤ ዕብራውያን 5:14 ምግባራችን። በምናደርገው ነገር ሁሉ ከራስ ወዳድነት ነፃ የሆነ ፍቅር ለማሳየት ጥረት እናደርጋለን። (ዮሐንስ 13:34, 35) ደም እንደ መውሰድ ካሉ አምላክን ከሚያሳዝኑ ድርጊቶች እንርቃለን። (የሐዋርያት ሥራ 15:28, 29፤ ገላትያ 5:19-21) ከሰዎች ጋር በሰላም የምንኖር ሲሆን በጦርነትም አንካፈልም። (ማቴዎስ 5:9፤ ኢሳይያስ 2:4) የምንኖርበትን አገር መንግሥት የምናከብር ሲሆን ከአምላክ ሕግ ጋር እስካልተጋጨ ድረስ የዚያን አገር ሕጎች እንታዘዛለን።—ማቴዎስ 22:21፤ የሐዋርያት ሥራ 5:29 ከሌሎች ጋር ያለን ግንኙነት። ኢየሱስ “ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ” የሚል ትእዛዝ ሰጥቷል። እንዲሁም ክርስቲያኖች “የዓለም ክፍል አይደሉም” በማለት ተናግሯል። (ማቴዎስ 22:39፤ ዮሐንስ 17:16) በመሆኑም ‘ለሁሉም ሰዎች መልካም ብናደርግም’ ከፖለቲካዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ ነን፤ ከሌሎች ሃይማኖቶች ጋር ኅብረት ከመፍጠርም እንርቃለን። (ገላትያ 6:10፤ 2 ቆሮንቶስ 6:14) ይሁን እንጂ በዚህ ረገድ ሌሎች የሚያደርጉትን ውሳኔ እናከብራለን።—ሮም 14:12 የክርስትና ክፍልፋዮች
12319
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B2%E1%89%AA%E1%88%8D%20%E1%8A%A2%E1%8A%95%E1%8C%82%E1%8A%90%E1%88%AA%E1%8A%95%E1%8C%8D
ሲቪል ኢንጂነሪንግ
ሲቪል ምህንድስና ወይም ሲቪል ኢንጂነሪንግ አንዱ እና ታዋቂው የምህንድሥና (ኢንጂነሪንግ) ዘርፍ ነው። ሲቪል ምህንድስና ስለ ግንባታ አካላት አስፈላጊነት ቅድመ ጥናት የሚያደርግ እንዲሁም የግንባታ አካላቱ አስፈላጊነት ከታመነበት በኋላ፤ የንድፍ ስራና የግንባታ ሂደትን የሚከታተልና የሚያስፈጽም እንዲሁም የግንባታ አካላቱ አገልግሎት ላይ ከዋሉ በኋላ የአገልግሎት እድሜያቸው እስከሚያበቃ ድረስ የሚፈለግባቸውን አገልግሎት እየሰጡ እንዲቆዮ የጥገና ስራዎችን የሚያጠናና የሚተገብር የሙያ ዘርፍ ነው። ከግንባታ አካላት ውስጥ መንገዶች፣ ድልድዮች፣ ህንጻዎች፣ ግድቦች፣ የአየር ማረፊያ አስፋልት ንጣፎች፣ የውሃ ተፋሰስ መስመሮች፣ ለተለያዮ አገልግሎቶች የሚውሉ ትቦዎች፣ የባቡር ሃዲዶች፣ ለትራንስፖርት አገልግሎት የሚውሉ ሰው ሰራሽ ወንዞች እና ሌሎችም ይገኙበታል። ሲቪል ምህንድስና በጥንታዊነት ከወታደራዊ ምህንድስና ቀጥሎ ሁለተኛውን ደረጃ ሲይዝ፣ የሙያ ዘርፉ የግንባታ አካላቱ ላይ እንዲሁም የግንባታ ሂደቱ ላይ ተሞርኩዞ በተለያዮ የሙያ ዘርፎች ይከፋፈላል። የሙያ ዘርፉም ከማህበረሰብ አገልግሎቶች ጀምሮ (ለምሳሌ እንደ መንገድ ግንባታ) እስከ ግለሰብ ደረጃ ድረስ (የግለሰብ መኖሪያ ቤት) የሚተገበር ነው። ሲቪል ምህንድስና የተፈጥሮ ህግጋትንና የሳይንስ መርሆችን በመጠቀም የአንድን ማህበረሰብ ተግዳሮቶች ለመፍታት የሚጥር የሙያ ዘርፍ በመሆኑ ታሪካዊ እድገቱ ከተፈጥሮ ህግጋት ሳይንስ (ቪዚክስ) እና ከሂሳብ ሳይንስ የግንዛቤ እድገት ጋር የተያያዘ ነው። ሲቪል ምህንድስና ዘርፍ፤ የአወቃቀር ሳይንስ ()፣ የከርሰ ምድር ሳይንስ፣ የአፈር ሳይንስ፣ የውሃ ሳይንስ () ፣ የአካባቢ ሳይንስ ፣ ሜካኒክስ (አንድ ቁስ በጫና አማካኝነት የሚያሳየው የለውጥ ሂደት የሚያጠና ዘርፍ ነው) ፣ የቁስ አወቃቀር ሳይንስ ()፣ የመልክዓ ምድር ሳይንስ እና የመሳሰሉትን ዘርፎች የሚያካትት ስለሆነ እድገቱም ከእነኚህ በውስጡ ከሚገኙ የሙያ ዘርፎች እድገት ጋር የተያያዘ ነው። ሲቪል ምህንድስና የሚያካትታቸው የአገልግሎት ዘርፎች ሲቪል ምህንድስና ሰፊ የሙያ ዘርፍ እንደመሆኑ በውስጡ ብዛት ያላቸው ሌሎች የሙያ ዘርፎችን ይይዛል። አማካሪ ሲቪል መሀንዲሶች () ከእነኚህ የተለያዮ የሙያ ዘርፎች በአንዱ ላይ ጠለቅ ያለ ስልጠናና ትምህርት ወስደው፤ በወሰዱት የስልጠና መስክ የአማካሪነት ሚና ሲኖራቸው፤ አጠቃላይ ሲቪል መሀንዲሶች () ደግሞ ስለ ሁሉም የሲቪል ምህንድስና ዘርፎች መሰረታዊ እውቀት ኖርዋቸው በተለያዮ ዘርፍሮች ከሰለጠኑት አማካሪ ሲቪል መሀንዲሶችና እንዲሁም የቅየሳ ባለሙያዎች ጋር በመሆን አንድን የተወሰነ የመሬት ይዞታን ከነበረበት የአገልግሎት ሁኔታ ወደሚፈለግበት የአገልግሎት ሁኔታ በግንባታ አማካኝነት የመለወጥ ስራን ያከናውናሉ። አጠቃላይ ሲቪል መሀንዲሶች አብዛኛውን ጊዜያቸውን የግንባታ ስራዎን በመጎብኘትና በመቆጣጠር፣ ከግንባታ አካላቱ ባለቤቶች፣ ስራ ተቋራጮችና ሌሎች ከግንባታ አካላቱ ጋር ግንኙነት ካላቸው አካላት ጋር በመገናኘትና ስለ ግንባታው ሂደት መረጃ በመለዋወጥ፤ የግንባታ እቅዶችን በማውጣትና በመቆጣጠር እንዲሁም ሌሎች ተዛማጅ ስራዎችን ለመስራት ያውላሉ። ሲቪል መሀንዲሶች የመሬት ምህንድስና ፣ የአወቃቀር ምህንድስና ፣ የአካባቢ ሳይንስ ምህንድስና ፣ የመጓጓዣ ምህንድስና ፣ የግንባታ ምህንድስና እና ሌሎች ተዛማጅ የምህንድስና መስኮችን በመጠቀም ለመኖሪያ ፣ ለንግድ፣ ለኢንዱስትሪ እንዲሁም ለማህበረሰብ አገልግሎቶች የሚውሉ አነስተኛ እንዲሁም ግዙፍ ግንባታዎችን ያከናውናሉ። ዋና ዋና የሲቪል ምህንድስና ዘርፎች የወደብ (የባህር ዳርቻ) ምህንድስና የወደብ ምህንድስና የወደብ አካባቢን የማልማትና የማስተዳደር ስራዎችን የሚያከናውን ሲሆን፣ ወደብን ለመጓጓዣ ስራ ከማዋል በተጨማሪ፣ በወደብ አካባቢ የሚከሰቱ የውሃ መጥለቅለቅ አደጋዎችን፣ የአፈር መሸርሸርና እና የመሳሰሉ የተፈጥሮ አደጋዎችን የመከላከል ስራ የሚያከናውን የምህንድስና ዘርፍ ነው። የግንባታ ምህንድስና የግንባታ ምህንድስና የግንባታ ሂደትን የማቀድ፣ የማስፈጸም፣ ለግንባታው የሚያስፈልጉ የግንባታ ቁሳቁሶችን የማጓጓዝና የማቅረብ፣ እንዲሁም የግንባታ ቦታውን ለሚፈለገው የግንባታ አካል እንዲውል በግንባታው አካባቢ የሚገኙ የተፈጥሮ ሀብቶች ጥበቃ መሟላቱን የማረጋገጥ፣ የግንባታ ቦታው ለግንባታ ስራ ደህንነትና ምቹነት ያለው መሆኑን የማረጋገጥ እንዲሁም አግባብ የሆነ የግንባታ መሬት አጠቃቀምን የሚከታተልና የሚያስፈጽም የምህንድስና ዘርፍ ነው። የግንባታ ተቋራጮች በሌሎች የሲቪል ምህንድስና አገልግሎቶች ላይ ከተሰማሩ የአገልግሎት ተቋሞች አንጻር የተሰማሩበት መስክ ከፍተኛ የንግድ አደጋ ወይም መዋዠቅ ስለሚከሰትበት የግንባታ መሃንዲሶች አብዛኛውን ጊዜያቸውን ንግድን በተመለከቱ ጉዳዮች ለምሳሌ ያህል የግንባታ ውሉን በመገምገም እና ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸውን ጉዳዮች በማርቀቅ፣ የግንባታ ግብአቶችን አቅርቦት ፍሰት በመቆጣጠር፣ እንዲሁም የግንባታ እቃዎች የገበያ ዋጋ መረጃን በመሰብሰብ ላይ ያውላሉ። የመሬት ርዕደት ምህንድስና የመሬት ርዕደት ምህንድስና መሬት ርዕደት በሚያይልባቸው አካባቢዎች የሚሰሩ የግንባታ አካላት፤ የመሬት ርዕደትን ተቋቁመው እንዲዘልቁ ለማድረግ የግንባታ አካላቱን አወቃቀር በተለየ መልኩ ትኩረት በመስጠት የሚያጠናና መፍትሄ የሚሰጥ የምህንድስና ዘርፍ ነው። ይህ የምህንድስና ዘርፍ የአወቃቀር ምህንድስና ዘርፍ አካል ነው። የመሬት ርዕደት ምህንድስና ዋነኛ አላማው በመሬትና በግንባታ አካሉ እንዲሁም በግንባታ አካላቱ መካካል በመሬት ርዕደት ጊዜ የሚኖረውን መስተጋብር መረዳትና የግንባታ አካሉ የመሬት ርዕደት ሂደቱን አልፎ አገልግሎት እንዲሰጥ አወቃቀሩን፣ የግንባታ ቁስ አመራረጡን እንዲሁም መሰል የግንባታ መፍትሄዎችን በየሀገራቱ ጥቅም ላይ ከዋሉ የግንባታ መስፈርቶች ጋር በሚስማማ መልኩ መተግበር ነው። የአካባቢ ጥበቃ ምህንድስና የአካባቢ ጥበቃ ምህንድስና ከጤና ጥበቃ ምህንስና ጋር ተጓዳኝ የሆነ የምህንድስና ዘርፍ ሲሆን፣ የጤና ጥበቃ ምህንድስና በአመዛኙ የንጹህ ውሃ መጠጥ አቅርቦትና የአካባቢ ቆሻሻ ፍሳሽ አወጋገድ ላይ ሲያተኩር፤ የአካባቢ ጥበቃ ምህንድስና ሰፋ ባለ መልኩ የአካባቢ ብክለት የሚያስከትሉና ለጤና ጠንቅ የሆኑ ጎጂ ኬሚካሎችን እና ቆሻሻዎችን መቆጣጠርና ማስወገድ ይጨምራል። የአካባቢ ጥበቃ ምህንድስና፤ የማህበረሰብ ጤና ምህንድስና እና የአካባቢ ጤና ምህንድስና በሚል አጠራርም ይታወቃል። የአካባቢ ጥበቃ ምህንድስና በኬሚካል ውህደቶች፣ በባዮሎጂካል ሂደቶች እንዲሁም በሙቀት ለውጥ አማካኝነት የሚፈጠሩ ቆሻሻዎችን የማጥራትና የማስወገድ፣ አየርንና ውሃን የማጣራት፣ እንዲሁም በአደጋ ወይም በቆሻሻ ክምችት የተበከለን የመሬት አካል ወደ ተፈጥሮዋዊ ይዘቱ የመመለስ ስራዎች የሚያከናወኑበት የምህንድስና ዘርፍ ነው። በአካባቢ ጥበቃ ምህንድስና ትኩረት ከሚደረግባቸው ዋና ነጥቦች ውስጥ የመርዝ ወይም የኬሚካል እንቅስቃሴ ወይም ጉዞ (ከመሬት ላይና ከመሬት በታች)፣ የውሃ ማጣራት፣ የቆሻሻ ፍሳሽ ማጣራት፣ የአየር ብክለት፣ የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድና የአደገኛ ቆሻሻዎች አያያዝ ይገኙበታል። የአካባቢ ጥበቃ መሃንዲሶች ብክለትን የመቀነስ፣ የአረንጓዴ ምህንድስና ዘርፍ ስራዎች (የአካባቢ ብክለትን የሚቀንሱ የግንባታ መንገዶችንና ቁሶችን የኢኮኖሚ አቅምን ባገናዘበ መልኩ የማጥናት ስራ)፤ እንዲሁም የኢንዱስትሪዎችን የቁሳቁስና የሃይል አጠቃቀም ፍሰት የማጥናት ስራዎችና () የመሳሰሉት ላይ ይሳተፋሉ። ከዚህም በተጨማሪ የአካቢቢ ጥበቃ መሃንዲሶች ድርጊቶች (ለምሳሌ የአንድ የግንባታ አካል ትግበራ) በአካባቢው ላይ ሊያስከትሉ የሚችሉትን ተጽእኖ በመገምገም መረጃ ያዘጋጃሉ። የምርመራ ምህንድስና የምርመራ ምህንድስና የግንባታ አካላት የሚፈለግባቸውን ጥቅም ሳይሰጡ ለአገልግሎት ከታቀደላቸው ጊዜ በፊት በመፍረስ አገልግሎት መስጠት ሲያቆሙ፣ እንዲሁም የመፍረስ አደጋው በሰው ወይም በንብረት ላይ አደጋ በሚያደርስበት ጊዜ የግንባታ አካሉን አወቃቀር ፣ የተሰራበትን ቁስ ፣ የግንባታውን ጥናት እንዲሁም መሰል ተዛማጅ ጉዳዮችን በመመርመር ተጠያቂ የሚሆነውን አካል ለማወቅና የፍርድ ሂደትን ለማገዝ የሚያገለግል የሲቪል ምህንድስና ዘርፍ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ይህ የምህንድስና ዘርፍ ከምርመራ ውጤቶች በመነሳት የግንባታ ቁሶችን ወይም የግንባታ አካላት ጥራትን እንዲሁም የግንባታ አካላት አወቃቀርን የማሻሻል ስራዎን ለመስራት የሚያስችል የሲቪል ምህንድስና ዘርፍ ነው። ልዮ የሆነ የባለቤትነት ፍቃድ () ያላቸውን የግንባታ ቁሶች ፣ አካላት ፣ ወይም የግንባታ ዘዴዎች የፍቃድ ባለቤቱን ይሁንታ ሳያገኙ በሚፈጸሙ ግንባታዎች ላይ የባለቤትነት ጥያቄዎችን ለመመለስ በሚደረጉ ህጋዊ ሂደቶች ላይ ይህ የምህንድስና ዘርፍ ቁልፍ ቦታ አለው። መሬት ነክ ምህንድስና (ጂኦቴክኒካል ምህንድስና) መሬት ነክ ምህንድስና የግንባታ አካላትን የሚሸከሙ አለቶችና አፈሮችን የምህንድስና ጠባይ የሚያጠና የሲቪል ምህንድስና ዘርፍ ነው። ይህ ዘርፍ ከአፈር ሳይንስ፣ ከቁስ ሳይንስ ፣ ከሜካኒክስ እንዲሁም የፍሰት ሳይንስ () እውቀቶችን በመጠቀም ደህንነታቸው የተጠበቀና የገንዘብ አቅምን ያገናዘቡ የግንባታ መሰረቶችን፣ የመጠበቂያ ግድግዳዎችን፣ ግድቦችን፣ ዋሻዎችን የመሳሰሉ የግንባታ አካላትን መንደፍና መገንባት ላይ ትኩረት ያደርጋል ። የከርሰ ምድር ውሃን በተለያዮ ምክንያቶች ከመበከል የመጠበቅ እንዲሁም የቆሻሻ ክምችትን በአግባቡ ለመቆለልና ክምችቱ የአፈርና የከርሰ ምድር ውሃን እንዳይበክል የማድረግ ስራዎችም በዚሁ የምህንድስና ዘርፍ የሚተገበሩ ናቸው። የአፈርን የምህንድስና ጸባይ የማወቅ ተግባር ለመሬት ነክ መሃንዲሶች ፈታኝ ነው። በሌሎች የሲቪል ምህንድስና ዘርፎች የግንባታ ቁሶች ጸባይ (ለምሳሌ እንደ ብረት እና ኮንክሪት) በሚገባ የሚታወቅ ሲሆን፤ በግንባታ አካባቢ የሚገኝን የአፈር ጸባይ ማወቅ ግን ከተለዋዋጭነቱና በናሙና በሚደረጉ ሙከራዎች መፈተሽ የሚቻለው ከጠቅላላውን የተወሰነውን ብቻ በመሆኑ በጣም አዳጋች ነው። ከዚህም በተጨማሪ አፈር በጭነት ምክንያት የሚያደርገው የቅርጽ ለውጥ ከጫናው ጋር ቀጥተኛ ያልሆነ () ተዛምዶ ስላለው፤ ማለትም አነስተኛ እና ከፍተኛ ለሆኑ ጫናዎች የተለያየ ጥንካሬ()፤ ጠጣርነት()፤ የቅርጽ ለውጥ ስለሚኖረው፤ የአፈርን የምህንድስና ጸባይ በተሟላ ሁኔታ ለማወቅ የዳግታል። መሬት ነክ መሃንዲሶች አብዛኛውን ጊዜ ከከርሰ ምድር ባለሙያዎችና የአፈር ሳይንቲስቶች ጋር በትብብር ይሰራሉ። የቁሶች ጥናት ሳይንስ ወይም ምህንድስና የቁሶች ጥናት ሳይንስ ወይም ምህንድስና በሲቪል ምህንድስና ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ሚና ይይዛል። የቁሶች ጥናት ሳይንስ ወይም ምህንድስና የቁሶችን ተፈጥሮዋዊ ባህሪ የሚያጠና የሳይንስ ወይም የምህንድስና ዘርፍ ነው። ለግንባታ ከሚውሉ ቁሳቁሶች ውስጥ ኮንክሪት፣ የአስፋልት ኮንክሪት፣ እንደ ብረት እና አልሙኒየም ያሉ ጠንካራ ብረታ ብረቶች ፣ የፕላስቲ ውጤቶችና የመሳሰሉት ይገኙበታል። የቁሶች ጥናት የግንባታ አካላትን ከተለያየ ጥቃት ለመከላከል የሚውሉ ቅባቶችና የመከላከያ ንጣፎችን፣ እንዲሁም አንድን የብረት አይነት ከሌላ የብረት አይነት ጋር በማደባለቅ ለግንባታ ተስማሚ የሆነ ሌላ አይነት የብረት አይነት ማምረት የመሳሰሉ ስራዎችንም ያጠቃልላል። የቁሶች ጥናት የትግበራ ፊዚክስና () የኬሚስትሪ እውቀቶችን የያዘ የምህንድስና ዘርፍ ነው። በቅርቡ እየተስፋፋ የመጣው የናኖ ሳይንስ ወይም ቴክኖሎጂን (ናኖ ሳይንስ የአንድን ቁስ የአቶምና የሞሎኪዮል አወቃቀር በመቀየር በተፈጥሮ የማይገኙ ለየት ያለ ባህሪ ያላቸውን ቁሶች ለመስራት የሚደረግ ጥረት ነው) ደረጃ ተንተርሶ በአሁኑ ጊዜ የቁሶች ጥናት ከፍተኛ የሆነ የምርምር ድርሻን ይዞ ይገኛል። የቁሶች ጥናት ምህንድስና በምርምር ምህንድስናና የግንባታ አካላት ከጥቅም ውጪ የመሆን መንስኤን ለማጥናት በሚደረጉ ስራዎች ላይ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። የአወቃቀር ምህንድስና (ስትራክቸራል ኢንጂነሪንግ) የአወቃቀር ምህንድስና የህንጻዎችን፣ የድልድዮችን፣ የማማዎችን፣ የመንገድ ማቋረጫ ድልድዮችን፣ የዋሻዎችን፣ በባህርና ላይ የሚገነቡ ለነዳጅ ወይም ለዘይት ማውጫ የሚያገለግሉ ሰው ሰራሽ መሬቶችን እና ማማዎችንና እንዲሁም እነኚህን የመሳሰሉ የግንባታ አካላትን በተመለከተ የአወቃቀር ንድፍና () የአወቃቀር ትንታኔ () ላይ የሚያተኩር የሲቪል ምህንድስና ዘርፍ ነው። የአወቃቀር ትንታኔ () ጉልበቶች በግንባታ አካላት ላይ የሚያሳድሩትን ተጽእኖ መመዘን ላይ ትኩረት ያደርጋል። የአወቃቀር ምህንድስና በግንባታ አካላት ላይ የሚያርፉ ጉልበቶችን ለምሳሌ የራሱ የግንባታ አካሉ ክብደት፣ በግንባታ አካሉ ላይ የሚያርፉ ሌሎች ቋሚና ተቀሳቃሽ ክብደቶች፣ የንፋስ ግፊት ፣ የሙቀት ለውጥ፣ የውሃ ግፊት፣ የመሬት ጫና፣ የመሬት ርእደት፣ በረዶ እና የመሳሰሉትን የመለየትና፣ በእነኝህ ጉልበቶች አማካኝነት በግንባታ አካላቱ ውስጥ የሚከሰቱ ውስጣዊ ጫናዎችንና ጉልበቶችን () የማስላትና የግንባታ አካላቱ እነኝህን ጉልበቶች ተቋቁመው አገልግሎት እንዲሰጡ መጠናቸውንና የሚሰሩበትን ቁስ መንደፍ ላይ ያተኩራል። የአወቃቀር ምህንድስና ባለሙያው የግንባታ አካላቱ ተጠቃሚዎችን ደህንነትን በሚጠብቅ መልኩ () እንዲሁም ግንባታ አካላቱ ከተሰሩበት አላማ አንጻር የሚጠበቅባቸውን አገልግሎት እንዲሰጡ አድርጎ () መንደፍ ይጠበቅበታል። እንደ ንፋስ እና የመሬት ርእደት አይነት ጉልበቶች በቀላሉ ለመተንበይ አስቸጋሪ በመሆናቸው በአወቃቀር ምህንድስና ስር እንደ ንፋስ ምህንድስና እና የመሬት ርእደት ምህንድስናን የመሳሰሉ ንኡስ ዘርፎች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆኖዋል። በአወቃቀር ምህንድስና ውስጥ የንድፍና የትንታኔ ስራ የግንባታ አካሉ ቋሚ ጉልበቶችን ፣ተለዋዋጭ ጉልበቶችን (እንደ ንፋስና የመሬት ርእደት ያሉ) ወይም ጊዜያዊ ጉልበቶችን (ለምሳሌ በግንባታ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውሉ የግንባታ ማሽኖች ክብደት፣ በግንባታ አካሉ ላይ በተንቀሳቃሽ ነገሮች አማካኝነት ሊከሰቱ የሚችሉ ግጭቶች እና የመሳሰሉት) ለመሸከም የሚያስፈልገውን ጥንካሬና ጠጣርነት መወሰን እንዲሁም የግንባታ አካሉ ሚዛኑን ጠብቆ መቆም መቻሉን ማረጋገጥ ያካትታል። ከዚህም በተጨማሪ የንድፍና ትንታኔ ስራ የግንባታውን ዋጋ መተመን፣ የግንባታውን ተግባራዊነት ማረጋገጥ፣ ግንባታው ውበት የተላበሰ መሆኑን ማረጋገጥ እንዲሁም የሃብት አጠቃቀምና የተፈጥሮ ሚዛንን በጠበቀ መልኩ ግንባታው እንዲከናውን ማስቻልን ያካትታል። ቅየሳ የአንድን የመሬት ገጽ ወይም የግንባታ አካል አቀማጥ ለማወቅ የሚደረግ የልኬት ስራ ነው። የቅየሳ ስራ ለቅየሳ ስራ የሚውሉ እንደ ውሃ ልክ () ወይም ቴዎዶላይት (አግድምና ሽቅብ ማእዘንን ለመለካት የሚችል አጉሊ መነጽር) ያሉ መሳሪያዎች በመጠቀም በሁለት የልኬት ቦታዎች መካከል ከልኬት ቦታው አንጻር የሚኖረውን የቦታ ልዮነት ለማወቅ የማእዘን () ፣ የአግድም ቁመትና የሽቅብ ቁመት ልኬቶችን በመውሰድና የሂሳብ ስሌትን በመጠቀም የመሬት ገጽን ወይም የግንባታ አካልን አቀማመጥ የመወሰን ተግባር ነው። ከኮምፒውተር እውቀት ማደግ ጋር በተያያዘ አውቶማቲክ የሆኑ እንደ የኤሌክትሪክ ርቀት መለኪያዎች በመፈልሰፋቸው እንደ ቶታል ስቴሽን፣ ጂፒኤስ፣ የጨረር ዳሰሳ () የመሳሰሉ መሳሪያዎች ባህላዊ የሆኑ መሳሪያዎችን በመተካት ላይ ናቸው። ትራንስፖርት ምህንድስና የትራንስፖርት ምህንድስና ሰዎችንና ቁሳቁስን ከቦታ ወደ ቦታ በደህንነት ፣ በተቀላጠፈና ምቹ በሆነ መንገድ ማጓጓዝ ላይ ትኩረት ያደርጋል። ይህንን አላማማ ለማሳካትም የመኪና፣ የባቡር፣ የውሃና የአየር ማረፊያ መንገዶች እንዲሁም የወደቦች ንድፍ፣ ግንባታና ጥገና ስራዎች በትራንስፖርት ምህንድስና ውስጥ ሰፊ ድርሻ ይይዛሉ። የትራንስፖርት ምህንድስና በውስጡ የትራንስፖርት ንድፍ ስራ () ፣ የትራንስፖርት ግንባታ እቅድ ()፣ የትራፊክ ምህንድስና ()፣ የከተማ ልማት ምህንድስና፣ የመንገድ ንጣፍ ምህንድስና የመሳሰሉ ንኡስ የሙያ ዘርፎችን የያዘ ነው። ሲቪል ኢንጂኔሪንግ
3497
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%96%E1%88%8B%E1%8A%95%E1%8B%B5
ፖላንድ
ፖላንድ ኃይለኛ የአውሮፓ ሀገር ነች። በዓለም ላይ ካሉት ካቶሊካዊ አገሮች አንዷ ስትሆን ከአውሮፓ ጠንካራ ወታደራዊ ሃይሎች አንዷ ነች። ፖላንድ የ1000 አመት ታሪክ ያላት ሀብታም ነች። የፖላንድ አባት በካርታው ላይ ከሌሉ 123 ፖላንድ በኋላ የፖላንድ ኮመንዌልዝ የመሰረተው ጆዜፍ ፒሱድስኪ ነው። የፖላንድ ታሪክ በተለምዶ የሚጀምረው በ966 ሲሆን የዋልታዎቹ መስፍን ሚሴኮ በተጠመቀ ጊዜ ነው። የፖላንድ ሕዝብ ምዕራባዊ የስላቭ ሕዝብ ሲሆን የጥንቶቹ የሳርማትያ ተዋጊዎች ዘር ነው። ሳርማትያውያን በ 5 ኛው ክፍለ ዘመን በቪስቱላ አቅራቢያ ያሉትን ክልሎች ድል አድርገው በጊዜ ሂደት ስላቪክ ሆኑ። እ.ኤ.አ. በ 1025 የፖላንድ ዱክ ቦሌስላው የፖላንድ ንጉስ ዘውድ ተደረገ። የፖላንድ ወዳጅ ከነበረው ከጀርመን ንጉሠ ነገሥት ኦቶ ሳልሳዊ ጋር ጠንካራ ትብብር ፈጠረ። ቦሌስዋው ከሞተ በኋላ የፖላንድ መንግሥት ወደ ብዙ ትናንሽ ዱኪዎች ተሰበረ። ለሁለት መቶ ዓመታት ፖላንድ የተሰበረ ግዛት ነበረች እና ከምዕራብ ለጀርመን ጥቃት የተጋለጠች ነበረች። ስለዚህም ፖላንድ የድሮውን የሲሌሲያ እና የፖሜራኒያ ክልሎቿን መቆጣጠር አቅቷታል። በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ንጉስ ውላዲስላው ዘ ሾርት አብዛኞቹን የፖላንድ የተሰበሩ ዱኪዎች (ማሶቪያ፣ ክራኮው፣ ታላቋ ፖላንድ እና ትንሹ ፖላንድ) አንድ ላይ በማገናኘት የፖላንድ ንጉስ በክራኮው፣ በዋወል ካቴድራል ውስጥ ዘውድ ተደረገ። አገሩ በጦርነትና በድህነት ተናጠች። በቅርቡ ሞንጎሊያውያን ፖላንድን በመውረር የክራኮውን ዋና ከተማ መሬት ላይ አቃጥለውታል። በ 1333 ከሞተ በኋላ ልጁ ካሲሚር አባቱ የተዋሃደውን ማጠናከር ጀመረ. በካሲሚር የህግ እና የጦር ሰራዊት ማሻሻያ ፖላንድ ጠንካራ እና የበለጸገች ሀገር ሆነች። ካሲሚር አሁን ታላቁ ካሲሚር በመባል ይታወቅ ነበር እናም ይህ ማዕረግ ያለው ብቸኛው የፖላንድ ንጉስ ይሆናል። ካሲሚር ምንም ወንድ ወራሾች አልነበሩትም ይህም የፖላንድ የፒያስት ሥርወ መንግሥት ማብቃቱን ያመለክታል። ጃድዊጋ የፖላንድ ንግስት ሆነች እና የሊትዌኒያን ግራንድ መስፍን ካገባች በኋላ በፖላንድ መንግስት እና በሊቱዌኒያ ግራንድ ዱቺ መካከል የግል ህብረት ፈጠረች። የፖላንድ-ሊቱዌኒያ ህብረት በ1569 የፖላንድ-ሊቱዌኒያ ኮመንዌልዝ ሆነ ወይም የመጀመሪያዋ የፖላንድ ሪፐብሊክ በመባልም ይታወቃል። ንጉሱ እና ፓርላማው በፈረሰኞቹ ተመርጠዋል። ከዓለማችን በጣም ዲሞክራሲያዊ እና ኃያላን አገሮች አንዷ ነበረች። በ 1610 የፖላንድ-ሊቱዌኒያ ሪፐብሊክ ሠራዊት ሞስኮን ድል አደረገ. በ1683 አውሮፓን ከንጉሣቸው ጃን ሶቢስኪ ጋር ባደረገው ጦርነት ቪየና ከነበረው የኦቶማን ወረራ ያዳኑት በጣም ታዋቂው ክፍል ክንፉ ሁሳርስ ነበሩ። እንደ አለመታደል ሆኖ እጅግ በጣም ሰላማዊ የፖላንድ-ሊቱዌኒያ ኖብል ሪፐብሊክ በ 18 ኛው ክፍለ ዘመን በክፉ ጎረቤቶቿ ፕራሻ, ኦስትሪያ እና አረመኔያዊው የሩሲያ ግዛት ተከፈለ. የቅርብ ጊዜ ታሪክ ሞስኮቪያውያን የፖላንድ ሲቪሎችን ጨፍጭፈው የፖላንድ ልሂቃንን ገደሉ። መላው የ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ለፖላንድ የነፃነት ትግል ነበር ፣ እስከ መጨረሻው 1914 ታላቁ ጦርነት ፈነዳ። የቅርብ ጊዜ ታሪክ የፖላንድ ሌጌዎንስ መሪ የነበረው ጆዜፍ ፒሱድስኪ በጦርነቱ አብዛኛው የፖላንድ ግዛት እንደገና በመግዛቱ በአዋቂነቱ በ1918 ነፃነቱን አገኘ። ፒስሱድስኪ በብዙዎች ዘንድ እንደ ፖላንድ ሰው ይታይ ነበር። ዳግም የተወለደችው የፖላንድ ሪፐብሊክ ብዙ የፖለቲካ ችግሮች ነበሩባት። የመጀመሪያው የተመረጠው ፕሬዝዳንት በ1922 በፖላንድ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ በመባል በሚታወቁት የሩሲያ ወኪሎች ተገድለዋል። ፒሱድስኪ አገሩን ማዳን እና ጉዳዩን በእጁ እንደሚወስድ ያውቃል። እ.ኤ.አ. በ 1926 ፒሱሱድስኪ በሙስና በተሞላው መንግስት ላይ አብዮት በመምራት የፖላንድን ማህበረሰብ ፣ ጤና እና ቅልጥፍናን የሚያሻሽል የ መንግስትን አቋቋመ። አሁንም ዲሞክራሲ ነበር ነገር ግን ከጠንካራ የሞራል መሪ ጋር። እንደ አለመታደል ሆኖ ይህ አዲስ የፖላንድ ነፃነት በ1939 ናዚ ጀርመን እና ሶቭየት ህብረት ፖላንድን በመውረር ብዙ ህዝቦቿን ከመግደላቸው በፊት 20 ዓመታት ብቻ ቆይቷል። መንግስት በስደት መልሶ መደራጀት ችሏል እንጂ እጁን አልሰጠም። የፖላንድ ወታደሮች በጦርነቱ በሁሉም ግንባር አልፎ ተርፎም በሀገሪቱ ውስጥ በድፍረት ተዋግተዋል። እ.ኤ.አ. በ 1944 በዋርሶው በጀርመኖች ላይ የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ አመጽ በጦርነቱ ወቅት በአውሮፓ ውስጥ ትልቁ አመፅ ነበር። የፖላንድ ሕዝብ ብዙ የዘር ማጥፋት ወንጀል ደርሶበታል፡- ሆሎኮስት፣ ካትይን፣ የዎልዪን እልቂት እና ሌሎች በርካታ እልቂቶች በጀርመኖች፣ ዩክሬናውያን፣ ሩሲያውያን እና ሊቱዌኒያውያን ጭምር የተፈጸሙ ናቸው። የፖላንድ ድንበሮች በጭካኔ ወደ ምዕራብ ተንቀሳቅሰዋል፣ እና ፖላንድ እንደ ዊልኖ እና ሎቭ ያሉ አስፈላጊ ከተሞችን አጥታለች። በ 1945 ከጦርነቱ ማብቂያ በኋላ ሶቪየቶች የቀሩትን የሀገር ውስጥ ሰራዊት ገደሉ እና አገሪቷን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠሩ ። እ.ኤ.አ. እስከ 1989 ፖላንድ በኮሚኒስቶች ላይ የተነሳው ህዝባዊ ሰላማዊ አመጽ የኮሚኒስት አገዛዝን አብቅቶ የምስራቃዊው ቡድን መፍረስ እስኪጀምር ድረስ ፖላንድ በሶቭየት ህብረት ተያዘች። አሁን ፖላንድ የበለጸገች እና በፍጥነት በማደግ ላይ ያለች ሀገር ነች።
9601
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%8B%B0
ተረት ደ
ደሀ ሰው ዶሮ ካረደ ከሁለት አንዳቸው ቢታመሙ ነው ደህና ሲታጣ ይመለመላል ጎባጣ ደህና ወገን ያጣ ወየው ያለበት ጣጣ ደህና ጦር ያለው ለግምብ ይሞክረው ደመና ለዝናብ ድግስ ለሆዳም ደመና በሰማይ የጨዋ ልጅ በአደባባይ ደመናን የጨበጠ ሰማይን የቧጠጠ የለም ደመወዙ ስንዴ ስራው ምን ግዴ ደመወዝ ያጣ ሎሌ ይኮበልላል በሀምሌ ደም ቢያለቅሱ ድንጋይ ቢነክሱ ደም ተቀብቶ ዝንብ አይፈሩም ደም ተቃብቶ ዝንብ አይፈሩም ደም ተበክለህ ዝንብን አትጥላ ደም ከውሀ ይቀጥናል ደም ካልፈሰሰ ስርየት የለም ደሞዝተኛ አርፈህ ተኛ ደረስሁ ልጅ ፈላሁ ጠጅ ደረቅ ይቀመጠላል እርጥብ ይጎብጣል ደረቴን ቢያመኝ እግሬን አገመኝ ደረቴን ሲያመኝ እግሬን አገመኝ ደረጃ ለፍቶ መሄጃ ደስታና መከራ ቀኝና ግራ ደስታና መከራ ቀኝና ግራ ናቸው ደባ ራሱን ስለት ድጉሱን ደባ ራሱን ስለት ድጉሱን አያጣውም ደባል ሲስነብት ይሆናል ባለቤት ደባልና ሹመት ያለሰበብ አይሄድ ደብር ለላስታ ድግድግታ ለጌታ ደብተራ ሲኮራ እቤት ክርስቶያን ገብቶ ጭራ ይይዛል ደብተራ የዘኬ ጎተራ ደብተራ የዘኬ ጎተራ ዘኬውን ሲቋ ጥር አነቀው ነብር ደብተራና ተማሪ ሰናፊልና ሱሪ ደንቆሮ ከሚያጫውተኝ የሚሰማ ያውጋኝ ደንቆሮ የሰማ ለት ያብዳል ደወል ላንበሳ ባማረለት ታዲያ ማን ይሰርለት ደወል እንደ ጠዋቱ ትጮሀ ለች ደጃቸውን አይዘጉ ሰውን ሌባ ይላሉ ደጃቸውን ከፍተው ሰውን ሌባ ይላሉ ደጃፉን ጥሎ በጓሮ ይመጣል ደገኛ ሲያርስ ቆለኛ ያነፍስ ደጉ ነገር ሳያልቅ ክፉ መናገር ደግ ሰው ከንጀራው ቆርሶ ከወጡ አጥቅሶ ደግ ሳይበላ ክፉ ይመራ ደግ ጌታ ሲለግስ እንደ ፏፏቴ ያርስ ደግ ጎረቤት ውሻና ድመት ያሳድጋል ደግና ማለፊያ ትግልና ልፊያ ደግ አማችን መጦር ክፉ አማችን በጦር ደግ አባት እርስት ያቆማል ክፉ አባት እዳ ያቆያል ደግነት አይታረስ ልጅነት አይመለስ ደግ ጎረቤት እቃ አያስገዛም ደግ ጎረቤት ያወጣል ከመአት ደካማ ቀበሌ በአህያ ይወረራል ደፋር ሴት ጉልቻ ረግጣ ትወጣለች ደፋር ወጥ ያውቃል ደፋርና ጭስ መውጫ ቀዳዳ አያጣም ደፋርና ጭስ መውጫ አያጣም ደፋርና ጭስ ምን ያመጣሉ ደፋርና ጭስ ዝዋይ ገቡ ዱርዬ ያገባ በሬው በሰኔ ገደል የገባ ዱላ ለባለጌ ምርኩዝ ለአሮጌ ዱላ የሚጠላው ሸክላ ብቻ ነው ዱላን ይዞ ሌባን መጠየቅ ዱላ ይዞ ሌባን መጠየቅ ዱባ ባገሩ ጋን ያህላል አሉ ዱባና ቅል አበቃቀሉ ለየቅል ዱባና ቅል አበቃቀሉ አንድ ይመስላል አበላሉ ለየቅሉ ዱባና ቅል አብሮ ይበቅል አበላሉ ለየቅል ዱቄት ባመድ ይስቃል ዱጨት ባመድ ይስቃል ዲያቆን ሲጠግብ በጧፍ ይማታል ወይፈን ሲቦርቅ ድንበር ያፈርሳል ዲያቆን ከዘፈነ ፍየል ከቀዘነ ዲያቆን ከዘፈነ ፍየል ከቀዘነ መዳኛም የለው ዲያቢሎስ በክፋቱ ተወጋ ዳቢቱ ዳሩ ምን ይሆናል ሆነና ሆነና ዳር ሲፈታ መሀል ዳር ይሆናል ዳር ዳር ያለ በመሀል የከበረ ዳቦ ሲበሉ ልብ ልቡን ዳገት ሲወጡ ጥግ ጥጉን ዳቦ በገና ቡና በጀበና ዳቦ በወጥ በግዜር ማምለጥ ዳቦ ካልበሉት ድንጋይ ሎሚ ካልመጠጡት እንቧይ ዳቦ ያለ ቅርፊት ጠላ ያለ ምርጊት ዳቦውን ጎርሶ ደሙን አብሶ ዳተኛ በሬ ሀብታም ነው ዳኛ ለዳኛ ያወርሳል ጉም ተራራ ያለብሳል ዳኛ ምን ያደላ ከተረታ ሊበላ ዳኛ ምን ያደላ ከተረታው ሊበላ ዳኛ ሲመረምር ከራስ ይዞ እስከ እግር ዳኛ ሲቆጣ ማር ይዞ ከደጁ ዳኛ ሲያዳላ በዳኛ አህያ ሲያጋድል በመጫኛ ዳኛ ሳለ ተናገር ውሀ ሲጠራ ተሻገር ዳኛ ሲገኝ ተናገር ውሀ ሲጠራ ተሻገር ዳኛ ስበር በእጅ ክበር ዳኛ ቢንቁ የተያዘ እህልን ይወቁ ዳኛ ቢንቁ የተያዘ እህል ይወቁ ዳኛ ቢያዳላ በዳኛ አህያ ቢያጋድል በመጫኛ ዳኛ ቢያጋድል በዳኛ አህያ ቢያጋድል በመጫኛ ዳኛ አውጥቼ ዘንግ አቅንቼ ዳኛ አይነቀፍ እሳት አይታቀፍ ዳኛ ካዳላ ጭነት ቀላል ዳኛ የወል ምሰሶ የመካከል ዳኛ የወል ምሰሶ የማሃል ዳኛ የፈረደበት መርከብ የተሰበረበት ዳኛ የፈረደው ስለት የቀደደው ዳኛ ያደላበት እሳት የበላበት ዳኛ ያፈሰሱለት ፈረስ የከሰከሱለት ዳኛ ይመረምራል ጣዝማ ይሰረስራል ዳኛና በሬ ሀብታም ነው ዳኛ ፍርድ አይከላ እህል ጎታ ይሞላ ዳኛን ቢንቁ የተያዘ እህልን ይወቁ ዳኞች ከመረመሩ ይናገራል ምድሩ ዳኞች ከመረመሩ ይናገራል ምድሩ ይገናል ነገሩ ዳኞች ከመረመሩ ይገኛል ነገሩ ዳዊትን ያህል መዝሙር ጨለማን ያህል ጥቁር (የለም) ዳክዬን ከውሀው ፈረስን ከገለባው ዳኛ ሲገኝ ተናገር ውሀ ሲጠራ ተሻገር ዳገት ሲወጡ ጥግ ጥጉን ዳቦ ሲበሉ ልብ ልቡን ዳገት እርሙ ሜዳ ወንድሙ ድሀ ለወዳጁ አይሰንፍ ሀብታም ካለወዳጁ አይተርፍ ድሀ ሲቀልጥ አመድ አመድ ይሸታል ድሀ ሲቀመጥ እጁን ይዘህ አወዛውዘው ድሀ ሲቀማጠል ከወገቡ ቀምጠል ድሀ ሲቀማጠል ከወገቡ ቅምጥል ድሀ ሲቆጣ እግሩ ይፈናጠራል ድሀ ሲቆጣ እግሩ መንገድ ያሰልጣል ድሀ ሲቆጣ ከንፈሩ ያብጣል መንገዱን ያሰልጣል ድሀ ሲቆጣ መንገድ ያፈጥነዋል ድሀ ሲናገር ሬት ኮሶ ሀብታም ሲናገር የማር በሶ ድሀ ሲንቀባረር ያለቀሰ ይመስላል ድሀ ሲያገኝ ያጣ አይመስለውም ድሀ ቅቤ ወዶ ማን ሊሸከም ነዶ ድሀ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ኑሮ እከክ ይወረው ነበር ድሀ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ኖሮ እከክ ይጨርሰው ነበር ድሀ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ኖሮ እከክ በወረሰው ድሀ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ እከክ ይጨርሰው ነበር ድሀ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ እከክ በፈጀው ድሀ በሽታ አያውቅም ሀብታም ጤና የለውም ድሀ ተበድሎ ማሩኝ ይላል ቶሎ ድሀ ውሃውን ጠጥቶ እሳቱን ይሞቃል ሀብታም ስለገንዘቡ ይጨነቃል ድሀና ድመት ሊሞት ሲል ያምርበታል ድሀና ገበያ ሳይገናኙ ይሞታል ድሀ በአመዱ ንጉስ በዘውዱ ድሀ በጉልበቱ ባለጸጋ በሀብቱ ድሀ ቢናገር አያደምቅ ቢጨብጥ አያጠብቅ ድሀ ባይ አይኔን አመመኝ ድሀ ተበድሎ ማሩኝ ይላል ቶሎ ድሀ ተበድሎ ራሱ ይታረቃል ሀብታም በድሎ ተመልሶ ይስቃል ድሀ ከንቡ ይዳላ ድሀ ከንቡ ይዳራ ድሀ ካለቀሰ ቀኑ መች አነሰ ድሀ ካልሰራ ዶሮ ካልጫረ ድሀ ካልጋረ ዶሮ ካልጫረ ድሀ ካልዘራ ዶሮ ካልጫረ ድሀ ካልዘራ ዶሮ ካልጫረ (ማን ያበላው ነበረ) ድሀ ከርሻ ዳቦዬን ለማንሻ ድሀ የሚበላው እንጂ የሚከፍለው አያጣም ድሀ በጉልበቱ ባለጸጋ በሀ ብቱ ድሀ በጉልበቱ ባለጸጋ በከብቱ ድሀ ያልፍልኛል ይላል ጌታ ቀኑን ይቆጥራል ድሀ ያመልክት ዳኛ ያሟግት ድሀና ሹም ተሟግቶ ድንጋይና ቅል ተማትቶ የማይሆን ነው ከቶ ድሀና ጌታ ተሟግቶ ድንጋይና ቅል ተማትቶ የማይሆን ነው ከቶ ድሀ ምን ትሰራለህ እንጂ ምን ትበላለህ የሚለው የለም ድሀ ሲያስለቅሱ ከስላሴ ይወቀሱ መንግስተ ሰማያትን አይወርሱ ድሀ ቢያስለቅሱ ከስላሴ ይወቀሱ መንግስተ ሰማያትን አይወርሱ ድሀን ካስለቀሱ በስላሴ ዘንድ ይወቀሱ ድሀን ፈርቼ ደጄን በቀን ዘግቼ ድህነት ከአምላክ መስማማት ድህነት ከአምላክ መስተካከል ድል በመታደል ሙያ በመጋደል ድል የባለ እድል ድል እድል በአንድ ድልድል ድል ድል እድልህ እንዳይጎድል ድመት ላመሏ ዛፍ ላይ ትወጣለች ድመት መንኩሳ መናከሷን አትረሳ ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ ድመት በታች ከሆነች ውሻ ታሸንፋለች ድመትና ቁንጫ ባዶ ቤት ይወዳል ድመትና አይጥ እሳትና ጭድ ድመትን በቆሎ መጠርጠር ድመትን አይጥ ገደለቻት ወይ ጥቃት ወይ ጥቃት ድመት ውስጥ ውስጡን አውሬ ናት ድምቢጥ እንደ አቅሟ በብር ትታገማለች ድምቢጥ እንደ አቅሟ በብእር ትታገማለች ድምጽና ቁንጫ ባዶ ቤት ይወዳል ድሪቶ ከነቅማሉ መጥፎ ሰው ከነአመሉ ወዲያ በሉ ድሪያ የዝሙት ዋዜማ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ድርብርብ እንደ ደጋ ንብ ድርና ማግ ለሀጭና ልጋግ ድር ቢያብር ጋቢ ይሰራል ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ድርጎ ራቱ ድርጎ ቢቀር ሞቱ ድርጎ የለመደች መበለት ወተት ያየች ድመት ድርጭት ፈንጠር ምዝግዝግ ጎንደር ድሮም እንዳይሆን ነው የቄስ ልጅ መኮነን (አለ) ድሮም እንዳይሆን ነው የቄስ ልጅ መኮንን (አለ) ድሮ ካያታችን ካጤ ነው ትውልዳችን ድሮም ሌባ ሲሰርቅ እንጂ ሲካፈል አይስማማም ድስት ግጣሙን አያጣም ድበላ አንዳንድ ጊዜ ይበላ ድንቢጥ እንደ አቅሟ በብእ ር ትታገም ድንቀኛ ተኳሽ ድር ይበጥሳል ድንቁርና ከልብህ መካከል ተራራ ያህል ድንኳን ያየ ባለጌ ድንኳን ገልጦ ዙፋንን ረግጦ ድንኳን ገልጦ ዙፋን ረግጦ ድንኳን ገልጦ ዙፋን አጊጦ ድንገተኛ ስህተት የቁልቁለት ውድቀት ድንጋይ ለረገጠ ፍለጋ የለውም ውሀ ለጠጣ ሽታ የለውም ድንጋይ ላይ ተቀማጭ የባለጌ ተለጣጭ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ትልቅ ቤት ይሆናል ድንጋይ ቢያጎኗት ተመልሳ ካናት ድንጋይ ወርዶ እዘብጥ ያርፋል ያገኘው ይተርፋል ድንጋይ ሲያረጅ መጭ ያበቅላል ድንጋይ ወደ ሰማይ ቢወርወር ተመልሶ ምድር ድንጋይ ወደ ሰማይ ቢወርወር ተመልሶ ወደ ምድር ድግርና ገባር ሲተካከል ያምር ድግስ የሌለው ዋዜማ ምልክት የሌለው ዜማ ድጥ ማንሸራተቱን ባለጌ ማሽሟጠጡን አይተውም ዶማ ለመማሻ ማረሻ ለመፈለሻ ዶሮ ላትበላው ታፈስ ዶሮ ልጆቹዋን ይዛ ጓሮ ለጓሮ ዶሮ ባሏ ሲሞት ሞተች እጢስ ገብታ ዶሮ ሲሉ ሰምታ ሞተች እጢስ ገብታ ዶሮ ሲቀጣጥቧት በመጫኛ ጣሏት ዶሮ ሲደልሏት በመጫኛ ጣሏት ዶሮ በልቶ ብስና ጎመን በልቶ ጤና ዶሮ በልቶ ከብስና ጎመን በልቶ በጤና ዶሮ በልጅዋ አንጀት ትጫወታለች ዶሮ በማሰሮ ገደል ለዝንጀሮ ዶሮ በጋን ዶሮ ቢጠፋ ከቤቱ መነኮሰች እናቱ ዶሮ ቢጠፋ ካባቱ መነኮሰች እናቱ ዶሮ ቢያማት በሬ ተሳሉላት ዶሮ ብታልም ጥሬዋን ዶሮ ብትታመም በግ አረዱላት ዶሮና ቀበሮ ተገናኝተው ጓሮ ዶሮና ቀበሮ ተገናኝቶ ጓሮ ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጠልፈው ጣሏት ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት ዶሮን ሲያታልሏት አንቺ እሩጭ እኛ እንከተልሽ አሏት ዶሮን ሲያታልሏት ጥምር መንግስት አሏት ዶሮን ሲያታልሏት ፎቶ አነሷት ዶሮ አንዱን እንቁላል በወለደችበት ወታቦ ትሞላለች ዶሮ እቤት ውላ ዝናብ ትመታለች ዶሮ እኔ ባልበላው ጭሬ አላፈሰውም ወይ አለች ዶሮ እኔ ባልበላ ጭሬ አላፈስም ወይ አለች ዶሮ ከቆጥ በሬ ከጋጥ ዶሮ ከቤት ሆና ዝናም ይመታታል ዶሮ ከቤት ውላ ዝናብ ይመታታል ዶሮ ከጋጥ አህያ ከቆጥ ዶሮ ከጋጥ በሬ ከቆጥ ዶሮ ከጮኸ ሌሊት የለም ከደብረ ታቦር ወዲያ ክረምት የለም ዶሮ ከጮኸ ሌሊት ከደብረ ታቦር ወዲያ ክረምት የለም ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት ከቡሄ ወዲያ የለም ክረምት ዶሮ ካልበሏት አሞራ ናት ዶሮ ጭራ ማረጃዋን አወጣች ዶሮ ጭራ መታረጃዋን አወጣች ዶሮ ጭራ የምታወጣው ምስጢር ዶሮ ጭራ ጭራ አወጣች ማረጃዋን ካራ ዶክተር ሲበዛ በሽተኛ ይሞታል
10353
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%88%E1%8A%93
ገና
ገና የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት የሚከበርበት ቀን ነው። ስሙ የወጣ ከግሪክ /ቅሪስቶው/ገና ማለትም «የክርስቶስ ልደት» ነው። የከበረና የተመሰገነ ታላቅ የልደት በዓል ሆነ የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከከበረች ድንግል ማርያም የተወለደባት ዕለት ከበዓላት ሁሉ ተለይታ ከፍ ከፍ ያለች ናት ። ስለ ገና ክፍል ፩ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን የከበረ የልደትን በዓል በሁለት ቀኖች ያከብሩ ዘንድ በምክራቸው ተስማሙ ከወደኋላ ባለ በሃያ ስምንት ሌሊቱ የልደት በዓል ነው በሃያ ዘጠኝ መዓልቱ ጳጉሜን ስድስት በሆነ ጊዜ በዚያች ዓመት የልደት በዓል በሃያ ስምንት በመዓልት ይከበራል ። ጳጉሜን አምስት ከሆነ ግን በሃያ ዘጠኝ ይሆናል ስለዚህ የበዓላት ሁሉ ራስ የሆነ የከበረ የልደት በዓል በሁለቱ ቀኖች እንዲከበር አዘዙ ወሠኑ ። የበዓላት ራስ ስለሆነ ስለ ከበረ የልደት በዓል የከበረ ወንጌል እንዲህ አለ ። በንጉሡ በኄሮድስ ዘመን በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ጌታ ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ እነሆ የፍልስፍና ሰዎች ከምሥራቅ መጥተው ወደ ኢየሩሳሌም ደረሱ ። ኮከቡን በምሥራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መጥተናልና የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው እያሉ ። እሊህ ፈላስፎች ከበለዓም ወገን ናቸው እነርሱም በከዋክብት የሚፈላሰፉ ናቸው በመጽሐፋቸው በበለዓም መጽሐፍም የአይሁድ ንጉሥ ሊወለድ እንዳለው ተጽፎአል እርሱ በለዓም ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል ከእስራኤልም ንጉሥ ብሎ ነበርና ። ይቅር ባይ እግዚአብሔርም በረቀቀ ጥበቡ አለበማቸው በሚያምኑበትም ሳባቸው እነርሱ ከዋክብትን በመጠባበቅ የሚፈላሰፉ ናቸውና ይህንንም ኮከብ ገለጠላቸው በአዩትም ጊዜ ደስ አላቸው መልኩ በብዙ አይነት ልውጥ ነውና ። ሕፃን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን ይመስላል እርሱም በቀን ይጓዛል በሌሊትም ይሠወራል ከሰውም ሲገናኙ ይሠወርና ሲቆሙ በሌላ አንጻር ይገለጥላቸዋል ። እነርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርሱ ያ ኮከብ ተሠወራቸው እጅግ አዘኑ የሚያደርጉትንም አላወቁም ከዚህም በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገብተው ስለተወለደው ንጉሥ ጠየቁ ። የእሊህም ሰዎች ቊጥራቸው ሠላሳ ሽህ ነው ነገሥታቱ ሦስት ናቸው ለየእንዳንዱ ንጉሥ ዐሥር አሥር ሽህ ሠራዊት አለው ። ንጉሡ ኄሮድስም በሰማ ጊዜ ደነገጠ ኢየሩሳሌምም በመላዋ ከእርሱ ጋር ደነገጠች ። የካህናት አለቆችና የሕዝቡን ጸሐፊዎች ሁሉ ሰብስቦ ክርስቶስ በየት ይወለዳል ብሎ ጠየቃቸው ። በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ነው አሉት በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና ። የኤፍራታ ዕፃ ቤተልሔም አንቺም ከይሁዳ ነገሥታት አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ካንቺ ይወለዳልና ። ከዚህም በኋላ ኄሮድስ ሰብአ ሰገልን በጭልታ ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከነሱ ተረዳ ። ሒዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር እርግጡን መርምሩ ያገኛችሁትም እንደሆነ እኔም መጥቼ እሰግድለት ዘንድ በኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ ብሎ ወደ ቤተልሔም ሰደዳቸው ። የነገራቸውንም ሰምተው ከንጉሡ ሔዱ እነሆ በምሥራቅ ያዩት ከከብ ወደ ቤተልሔም እስኪያደርሳቸው ይመራቸው ነበር ሕፃኑ ካለበትም ዋሻ ላይ ደርሶ ቆመ ። ክፍል ፪ ኮከቡንም ባዩ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር አገኙት ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥናቸውንም ከፍተው ወርቅ ከርቤ ዕጣን እጅ መንሻ አቀረቡለት ። በእግዚአብሔርም ፈቃድ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑ ጌታ ኢየሱስም በዚያች ዕለት ወደ ቤተልሔም መጡ ስለዚህም ሰብአ ሰገል አገኙአቸው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ናዝሬት በሌላ ቦታ አላደገምና ከተወለደም ዕድሜው ሁለት ዓመት ሆኖት ነበር አምላክ ነውና ስለ መንግሥቱ ወርቅን ገበሩለት ክህነትም ገንዘቡ ነውና ዕጣንን ገብሩለት ማሕየዊ ለሆነ ሞቱ ምልክትም ከርቤን ገበሩለት ። ወደ ኄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ነገራቸው በሌላ መንገድም ወደ አገራቸው ተመልሰው ገቡ ። አምላክ በሥጋ ስለመገለጡ ዓዋጅ ነጋሪዎችና ሰባኪዎች ሆኑ ። ይችም ዕለት ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት ስለርሷ የተናገረላት ናት እንዲህ ብሎ እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅን ትወልዳለች ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው ። ስለዚችም የከበረች ድንግል ነቢይ ሕዝቅኤል እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ እግዚአብሔርም አለኝ ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች አትከፈትም የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር አለ ። ነቢዩ ዳንኤልም አለ ሌሊት በራእይ አየሁ እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ ዘመኑን ወደ ሚያስረጅ ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት የዘላለም አገዛዝ ጌትነት መንግሥት ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው ። ዳግመኛም ኢሳይያስ እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጸልኝ አለ ። አሁንም ደግሞ አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ አለ ሁለተኛም ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል አለ ። ዳግመኛም ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶልናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው ። ስሙም ድንቅ መካር የዘላዓለም አባት የሰላም አለቃ ይባላል አለ ። ኤርምያስም አለ እግዚአብሔር እንዲህ አለ በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል እግዚአብሔርም ያመኑበትን ያድናቸዋል ። ኤልሳዕም እንዲህ አለ ። እ ግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል ። ናሆም ነቢይም እንዲህ አለ ። እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል ልብሱም እንደልብሴ ነው። ክፍል ፫ ነቢዩ ኢዩኤልም እንዲህ ተናገረ የእግዚአብሔር ዙፋን የሆነች ብላቴና ድንግልን አየሁ እርሷም እንደ እሳት ያልባት ነበር ስለርሷም ይቺ ማን ናት ብዬ ኪሩብን ጠየቅሁት ከአዳም ልጆች የተመረጠች የእግዚአብሔር ዙፋን ይህች ድንግል ናት በርሷም የተጐሳቈሉ አሕዛብ ይድናሉ ለአመነባትም ረድኤትና መጠጊያ ናት ። ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ አለ እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ ዛሬም በተዋሕዶ ወለድኩህ አለኝ ። ለምነኝ አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው ። ዳግመኛም አብ አለ ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ካንተ ጋራ ሳለሁ ከአጥቢያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለሙ አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ ከማለም አይጸጸትም ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ ለእስራኤልም በበረሀ ውስጥ ከኅቱም አለት ውኃ እንደ ፈለቀ የደነቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደ አፈራች ። በሶምሶንም እጅ ውስጥ ከአህያ መንጋጋ ዐጥንት ውኃ እንደ ፈሰሰ ። እንዲሁ የጌታችን ልደት በኅቱም ድንግልና ሆነ ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደ ነደደች ዕፂቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁ የመለኮቱ እሳት ድንግልን አላቃጠላትም ። ለርሱም ከቸር አባቱ ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነት ክብር ምስጋና ሰጊድ ከርሱ ጋር በትክክልነት ይገባል ለዘላለሙ አሜን ። የኢትዮጵያ በዓላት
12248
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%88%AC%E1%89%B5
መሬት
መሬት (ምልክት፦) ከፀሀይ ሶስተኛዋ ፕላኔት ናት እና ህይወትን በመያዝ የሚታወቀው ብቸኛው የስነ ፈለክ ነገር ነው። በፀሃይ ስርአት ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው ውሃ ሊገኝ ቢችልም, ምድር ብቻ ፈሳሽ ውሃን ታስተናግዳለች. 71% የሚሆነው የምድር ገጽ ከውቅያኖስ ነው የተሰራው፣ የምድር ዋልታ በረዶ፣ ሀይቆች እና ወንዞች። ቀሪው 29% የምድር ገጽ መሬት ነው ፣ አህጉራትን እና ደሴቶችን ያቀፈ። የምድር የላይኛው ክፍል የተራራ ሰንሰለቶችን፣ እሳተ ገሞራዎችን እና የመሬት መንቀጥቀጦችን ለማምረት መስተጋብር ከበርካታ ቀስ ብለው በሚንቀሳቀሱ ቴክቶኒክ ፕላቶች የተሰራ ነው። የምድር ፈሳሽ ውጫዊ ኮር የምድርን ማግኔቶስፌር የሚቀርጸውን መግነጢሳዊ መስክ ያመነጫል፣ አጥፊ የፀሐይ ንፋስን ያስወግዳል። የምድር ከባቢ አየር በአብዛኛው ናይትሮጅን እና ኦክስጅንን ያካትታል. ከዋልታ ክልሎች የበለጠ የፀሐይ ኃይል በሞቃታማ ክልሎች ይቀበላል እና በከባቢ አየር እና በውቅያኖስ ዝውውር እንደገና ይሰራጫል። የውሃ ትነት በከባቢ አየር ውስጥ በሰፊው የሚገኝ ሲሆን አብዛኛውን ፕላኔቷን የሚሸፍኑ ደመናዎችን ይፈጥራል። እንደ ካርቦን ዳይኦክሳይድ ያሉ በከባቢ አየር ውስጥ ያሉ የግሪን ሃውስ ጋዞች ከፀሃይ ወደ ላይ ከሚገኘው የኃይል ክፍል ይጠመዳሉ። የአንድ ክልል የአየር ንብረት የሚተዳደረው በኬክሮስ ነው፣ ነገር ግን ከፍታ እና ወደ መካከለኛ ውቅያኖሶች ቅርበት ነው። እንደ ሞቃታማ አውሎ ነፋሶች፣ ነጎድጓዶች እና የሙቀት ሞገዶች ያሉ ከባድ የአየር ሁኔታ በአብዛኛዎቹ አካባቢዎች ይከሰታሉ እና ህይወትን በእጅጉ ይጎዳሉ። ምድር ወደ 40,000 ኪ.ሜ አካባቢ የሆነ ዔሊፕሶይድ ነች። በሶላር ሲስተም ውስጥ በጣም ጥቅጥቅ ያለ ፕላኔት ነው። ከአራቱ ዓለታማ ፕላኔቶች ትልቁ እና ግዙፍ ነው። ምድር ከፀሀይ ስምንት የብርሀን ደቂቃዎች ርቃ ትዞራለች፣ አንድ አመት ወስዳለች (365.25 ቀናት አካባቢ) አንድ አብዮት ለመጨረስ። ምድር በቀን ውስጥ በራሷ ዘንግ ዙሪያ ትዞራለች። የምድር የመዞሪያ ዘንግ ከፀሐይ ጋር ካለው የምሕዋር አውሮፕላኑ አንፃር ዘንበል ይላል፣ ወቅቶችን ይፈጥራል። ምድር በ 380,000 ኪሜ (1.3 ቀላል ሰከንድ) የምትዞረው በአንድ ቋሚ የተፈጥሮ ሳተላይት ጨረቃ ትዞራለች እና እንደ ምድር ሩብ ያህል ስፋት አለው። ጨረቃ ሁል ጊዜ ወደ ምድር በአንድ ጎን ትይዛለች ማዕበል በመቆለፍ እና ማዕበልን ያስከትላል ፣ የምድርን ዘንግ ያረጋጋል እና ቀስ በቀስ ሽክርክሯን ይቀንሳል። «አብርሃማዊ» በተባሉት ሃይማኖቶች (በተለይ ክርስትና፣ እስልምናና አይሁድና) ቅዱሳን መጻሕፍት እንደሚሉ፣ መጀመርያ ፪ ሰዎች አዳምና ሕይዋን ከኤደን ገነት ወጥተው የሰው ልጅ ታሪክ ከ6 ሺህ አመታት በላይ ብዙ አይሆንም። ከዚያ አስቀድሞ በገነት ያለፈው ዘመን ልክ ባይቆጠረም፣ ፍጥረቱ ከነምድርና ፀሐይ በ፯ «ጧቶች»ና «ምሽቶች» እንደ ተፈጸመ ስለሚባል፣ ባንድ ሳምንት ውስጥ እንደ ሆነ የሚያምኑ አሉ።ይሁን እንጂ ሳይንቲስቶች ምድር ከ4.6 ቢሊዮን ዓመታት በፊት እንደተፈጠረች ይናገራሉ፣ነገር ግን ይህ በኬንት ሆቪንድ ሳይንቲስቶች አጥብቆ ውድቅ የተደረገበት የይገባኛል ጥያቄ ነው። ሥርወ ቃል ምድር የሚለው ዘመናዊ የእንግሊዝኛ ቃል በመካከለኛው እንግሊዘኛ በኩል አዳበረ፣ ከአሮጌው የእንግሊዝኛ ስም ብዙ ጊዜ ተብሎ ይፃፋል። በሁሉም የጀርመንኛ ቋንቋዎች ውስጥ መግባቢያዎች አሉት፣ እና የአያት ሥሮቻቸው እንደ * እንደገና ተሠርተዋል። በመጀመሪያ ምስክርነቱ፣ የሚለው ቃል የላቲን ቴራ እና የግሪክ በርካታ ስሜቶችን ለመተርጎም ቀደም ሲል ጥቅም ላይ ውሏል፡ መሬቱ፣ አፈሩ፣ ደረቁ መሬት፣ የሰው አለም፣ የአለም ገጽ (ባህርን ጨምሮ) እና ሉል ራሱ ። ልክ እንደ ሮማን ቴራ/ቴሉስ እና ግሪክ ጋያ፣ ምድር በጀርመን ጣዖት አምላኪነት የተመሰለች አምላክ ሊሆን ይችላል፡ የኋለኛው የኖርስ አፈ ታሪክ ጆርዱ ('ምድር')ን ጨምሮ፣ ብዙ ጊዜ የቶር እናት ሆና የምትሰጥ ግዙፍ ሴት ናት። በታሪክ፣ ምድር በትንንሽ ሆሄ ተጽፋለች። ከመጀመሪያው መካከለኛው እንግሊዘኛ፣ “ግሎብ” የሚለው ትክክለኛ ትርጉሙ እንደ ምድር ይገለጻል። በቀድሞው ዘመናዊ እንግሊዝኛ፣ ብዙ ስሞች በካፒታል ተጽፈው ነበር፣ እና ምድርም እንዲሁ በምድር ላይ ተጽፏል፣ በተለይም ከሌሎች የሰማይ አካላት ጋር ሲጣቀስ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፣ ስሙ አንዳንድ ጊዜ በቀላሉ ምድር ተብሎ ይሰጠዋል፣ ከሌሎቹ ፕላኔቶች ስሞች ጋር በማመሳሰል፣ ምድር እና ቅርጾች ግን የተለመዱ ናቸው። የቤት ስልቶች አሁን ይለያያሉ፡ የኦክስፎርድ አጻጻፍ ትንሽ ሆሄ በጣም የተለመደ እንደሆነ ይገነዘባል፣ በአቢይ ሆሄያት ደግሞ ተቀባይነት ያለው ልዩነት ነው። ሌላው ኮንቬንሽን እንደ ስም በሚገለጥበት ጊዜ “ምድርን” አቢይ ያደርገዋል (ለምሳሌ “የምድር ከባቢ አየር”) ነገር ግን ከ (ለምሳሌ “የምድር ከባቢ አየር”) ሲቀድም በትንሽ ፊደላት ይጽፋል። ሁልጊዜ ማለት ይቻላል በትናንሽ ሆሄያት ይታያል እንደ "በምድር ላይ ምን እያደረክ ነው?" አልፎ አልፎ፣ ቴራ / / የሚለው ስም በሳይንሳዊ ፅሁፎች እና በተለይም በሳይንስ ልቦለድ ውስጥ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ፕላኔት ከሌሎች ለመለየት ጥቅም ላይ ይውላል ፣ በግጥም ውስጥ ቴሉስ / / የምድርን አካል ለማመልከት አገልግሏል። ቴራ በአንዳንድ የፍቅር ቋንቋዎች (ከላቲን የተሻሻሉ ቋንቋዎች) እንደ ጣሊያንኛ እና ፖርቱጋልኛ የፕላኔቷ ስም ሲሆን በሌሎች የሮማንቲክ ቋንቋዎች ቃሉ በትንሹ የተቀየረ ሆሄያት (እንደ እስፓኒሽ ቲዬራ እና ፈረንሳዊው ቴሬ) ስሞች እንዲፈጠሩ አድርጓል። የላቲን መልክ ወይም (እንግሊዝኛ: / /) የግሪክ የግጥም ስም ; ጥንታዊ ግሪክ: [] ወይም ምንም እንኳን አማራጭ አጻጻፍ የተለመደ ሆኗል ምክንያቱም የጋይያ መላምት፣ በዚህ ሁኔታ አጠራሩ // ከጥንታዊው እንግሊዝኛ // ይልቅ ነው። ለፕላኔቷ ምድር በርካታ ቅጽል ስሞች አሉ። ከምድር እራሱ ምድራዊ ነው። ከላቲን ቴራ ተርራን //፣ ምድራዊ //፣ እና (በፈረንሳይኛ በኩል) ተርሬን //፣ ከላቲን ቴሉስ ደግሞ ቴልዩሪያን // እና ቴልዩሪክ ይመጣሉ። የዘመን አቆጣጠር የምድር ከባቢ አየር እና ውቅያኖሶች የተገነቡት በእሳተ ገሞራ እንቅስቃሴ እና በጋዝ መውጣት ነው። ከእነዚህ ምንጮች የሚወጣው የውሃ ትነት ወደ ውቅያኖሶች ተጨምቆ፣ ከውሃ እና ከአስትሮይድ፣ ከፕሮቶፕላኔቶች እና ከኮሜትዎች የተነሳ በረዶ ተጨምሮበታል። ውቅያኖሶችን ለመሙላት በቂ ውሃ ከተፈጠረ ጀምሮ በምድር ላይ ሊሆን ይችላል. በዚህ ሞዴል በከባቢ አየር ውስጥ ያሉ የግሪንሀውስ ጋዞች አዲስ የተቋቋመው ፀሐይ አሁን ካላት ብርሃን 70% ብቻ በነበራት ጊዜ ውቅያኖሶች እንዳይቀዘቅዝ አድርገዋል። በ 3.5 ጋ ፣ የምድር መግነጢሳዊ መስክ ተመስርቷል ፣ ይህም ከባቢ አየር በፀሐይ ንፋስ እንዳይወሰድ ረድቷል ። የቀለጠው የምድር ሽፋን ሲቀዘቅዝ የመጀመሪያውን ጠንካራ ቅርፊት ፈጠረ፣ እሱም በአቀነባበሩ ውስጥ በጣም ጥሩ ነው ተብሎ ይታሰባል። በዚህ የማፊያ ቅርፊት ከፊል መቅለጥ የተፈጠረው የመጀመሪያው አህጉራዊ ቅርፊት ፣ በአፃፃፍ ውስጥ የበለጠ ፈልሳፊ ነበር። በ ዓለቶች ውስጥ የሃዲያን ዘመን የማዕድን ዚርኮን እህሎች መኖራቸው ቢያንስ አንዳንድ ፍልሰት ቅርፊት እንደ 4.4 ጋ ፣ ምድር ከተፈጠረች በኋላ 140 ብቻ እንደነበረ ይጠቁማል። ይህ የመጀመሪያ አነስተኛ መጠን ያለው አህጉራዊ ቅርፊት አሁን ያለበትን ብዛት ለመድረስ እንዴት እንደ ተለወጠ የሚያሳዩ ሁለት ዋና ሞዴሎች አሉ፡ እስከ ዛሬ ድረስ በአንጻራዊነት የተረጋጋ እድገት፣ ይህም በአለም አቀፍ ደረጃ በአህጉራዊ ቅርፊት ባለው ራዲዮሜትሪክ እና የመጀመርያ ፈጣን እድገት በአርኪያን ጊዜ በአህጉራዊ ቅርፊት መጠን ውስጥ ፣ አሁን ያለውን የአህጉራዊ ቅርፊት ጅምላውን ይፈጥራል ፣ ይህም በዚርኮን እና ኒዮዲሚየም በዚርኮን ውስጥ ባለው ማስረጃ የተደገፈ ነው። ሁለቱ ሞዴሎች እና እነርሱን የሚደግፉ መረጃዎች በተለይም የምድር ታሪክ የመጀመሪያ ደረጃዎች ላይ በትልቅ አህጉራዊ ቅርፊት እንደገና ጥቅም ላይ በማዋል ሊታረቁ ይችላሉ. አዲስ አህጉራዊ ቅርፊት በፕላስቲን ቴክቶኒክስ ምክንያት ይፈጠራል፣ ይህ ሂደት በመጨረሻ ከምድር ውስጠኛው ክፍል በሚመጣው የማያቋርጥ ሙቀት ማጣት የተነሳ ነው። በመቶ ሚሊዮኖች በሚቆጠሩ አመታት ውስጥ የቴክቶኒክ ሃይሎች የአህጉራዊ ቅርፊቶችን አንድ ላይ በመቧደን በኋላ የተበታተኑ ሱፐር አህጉራትን እንዲፈጥሩ አድርገዋል። በ 750 ማ አካባቢ ከመጀመሪያዎቹ ከሚታወቁት ሱፐር አህጉራት አንዱ የሆነው ሮዲኒያ መለያየት ጀመረ። አህጉራቱ እንደገና ተዋህደው ፓኖቲያ በ600–540 ፣ በመጨረሻም ፓንጋያ፣ እሱም በ180 መለያየት ጀመረ። በጣም የቅርብ ጊዜው የበረዶ ዘመን ንድፍ ወደ 5,000 ዓመታት ጀምሮ የጀመረ ሲሆን ከዚያም በፕሌይስቶሴን ጊዜ በ 3 አካባቢ ተጠናክሯል. ከፍተኛ እና መካከለኛ ኬክሮስ ክልሎች ከ 5,000 ዓመታት በፊት ባበቃው የምድር ሕይወት ውስጥ አንድ ጊዜ ያህል ደጋግመው የበረዶ ግግር እና የሟሟ ዑደቶች አልፈዋል። የመጨረሻው የበረዶ ግግር ጊዜ፣ በቋንቋው “የመጨረሻው የበረዶ ዘመን” ተብሎ የሚጠራው፣ ትላልቅ የአህጉራትን ክፍሎች፣ እስከ መካከለኛው ኬክሮስ፣ በበረዶ ውስጥ የሸፈነ እና ከ 5,000 ዓመታት በፊት ያበቃል። የሳይንስ ሊቃውንት የኖህ የጥፋት ውሃ ከታላቁ ጎርፍ እንዲወጣ የሚያደርጉ መሳሪያዎችን እንደሚፈጥር የበረዶ ሙቀትን እንደሚፈጥር ተናግረዋል ። እና የበረዶው ዘመን ታላቁ የጎርፍ ዘመን ይሆናል። የመሬት ውስጣዊ ክፍል መሬት በመዋቅሯ ከእንቁላል ጋር ተመሳሳይ መዋቅር አላት። ውስጣዊ እና ውጫዊ ይዘቷ ባጠቃላይ በሶስት ይከፈላል። ይህም በእንቁላል አካል የውጨኛው ቅርፊት፣ የመካከለኛው ፈሳሽ እና የውስጠኛው አስኳል ብለን እንደምንከፍለው በመሬትም ተመሳሳይ አቀማመጥ ያላቸው ክፍሎች አሉ። ውጫዊ የመሬት ክፍል የመጀመሪያው ውጫዊው የመሬት ክፍል ወይም በእንግሊዝኛው ክረስት የሚባለው ሲሆን የመሬት ቅርፊት ልንለው እንችላለን። በአብዛኛው ከተለያዩ የቋጥኝ አይነቶች የተገነባ ሲሆን ህይወት ያላቸው ነገሮች በሙሉ የሚኖሩት በዚህኛው የመሬት ክፍል ላይ ነው። ይህ ክፍል ውፍረቱን በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል። ምክንያቱ ደግሞ በውቅያኖሶች ስር ያለው የውፍረቱ መጠን እና በአህጉራት ላይ ያለው መጠን ስለሚለያይ ነው። የመሬት ቅርፊት በውቅያኖሶች ስር ያለው ውፍረት ከአምስት ሺህ ሜትር ( 3 ማይል) እስከ አስር ሽህ ሜትር ( 6 ማይል) ነው። ይህ ውፍረት በአህጉሮች ላይ ከሰላሳ ኪ.ሜ. (20 ማይል) እስከ ሃምሳ ኪ.ሜ. (30 ማይል) ነው። መካከለኛው የመሬት ክፍል ሁለተኛው የመሬት ክፍል መካከለኛው የመሬት ክፍል ወይም በእንግሊዝኛው ማንትል በመባል ይጠራል። ይህ የመሬት ክፍል ፈሳሻማ ይዘት አለው። ውፍረቱ እስከ 2890 ኪ.ሜ. (1800 ማይል) ይደርሳል። የመሬትን 84 በመቶ መጠን ይሆናል። በአብዛኛው በቅልጥ አለት ወይም ማግማ የተሞላ ነው። ይህም በእንቁላል የመካከለኛው ነጭ ፈሳሽ ይወከላል። ውስጠኛው የመሬት ክፍል የመጨረሻው እና ሶስተኛው ደግሞ ውስጠኛው የመሬት ክፍል ወይም በእንግሊዝኛው ኮር የሚባለው ነው። በእንቁላል የውስጠኛው አስኳል መወከል ይቻላል። እጅግ በጣም ሞቃት ሲሆን የፀሐይን የውጨኛ ክፍል መጠነ ሙቀት ይኖርዋል። ይህ ክፍል መጠኑ አነስተኛ ሲሆን በራዲየስ እስከ 1220 ኪ. ሜ. ብቻ ነው። በዚህም የጨረቃን መጠን 70 በመቶ ጋር ይነጻጸራል። የመሬት ታሪክ የመሬትን ታሪክ ለማወቅ የተፈጥሮ ሳይንስ የበኩሉን ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም የመሬት እድሜ ከ4.67 ቢሊዮን አመት ወዲህ ያሉትን አመታት በሙሉ የሚያጠቃልል ይሆናል። ይህም የጠቅላላ ሰማያዊ አካላት ወይም ዩኒቨርስን ሲሶ (አንድ ሶስተኛ) እድሜ ይሸፍናል። በዚህ ዘመን ነው እንግዲህ መልከዓ-ምድራዊም ሆነ ፍጥረታዊ ለውጦች የተከናወኑት። በአጠቃላይ የመሬትን ታሪክ ሳይንሳዊ በሆነ ወይም ሃይማኖታዊ በሆነ መልኩ ማየት ይቻላል። ሁለቱም በአሁኑ ጊዜ ተቀባይነት ያላቸው መላምቶች ናቸው። (ደግሞ «ባለሙያ ንድፍ»ን ይዩ።) የመጀመሪያው እና ከተመሰረተ ከሁለት ሺህ አመታት በላይ ያስቆጠሩት ሃይማኖታዊ እምነቶች አሉ። በነዚህ መሰረት መሬት የተፈጠረችው የአለም ፈጣሪና ጌታ በሆነው በእግዚአብሔር ወይም በአላህ ለሰው ልጆች መኖሪያ ተብሎ ነው የሚል እምነት አለው። ይህ እምነት በአብዛሃኛው የአለም ሃይማኖታዊ ህዝቦች ተቀባይነት ያለው ነው። ይዘቱም በተለያዩ የእምነት አይነቶች የተለያየ ፈጣሪ እንደመኖሩ የሚለያይ ነው። ለዚህ አስተሳሰብ ከሚወክሉት መሃል አንዱ የቅብጥ ተዋሕዶ ቄስ አባ ታድሮስ ማላቲ እንደሚሉት፣ በትምህርተ ሂሳብ ረገድ የመሬቲቱ ስፋት ለአንድ ሚልዮን አመታት የሰው ልጅ ትውልድ መበዛት በቂ ሊሆን ከቶ አይችልም። እያንዳንዱ ቤተሠብ በአማካኝ 3 ልጆች ብቻ ቢወልዱ በሚልዮን አመታት የመሬት ስፋት አንድ ሺህ እጥፍ ቢሆንም እንኳ አይበቃም ይላሉ። ስለዚህ የምድር እድሜ ስፍር ቁጥር የሌለው ረጅም ጊዜ ቢሆንም፣ የስው ልጅ ትውልድ ግን ከ6000 ሺህ አመታት በላይ ብዙ ሊሆን አይችልም ይላሉ። ይህ ቲዎሪ የተመሰረተው ሳይንስ ካገኛቸው የመሬት ላይ መረጃዎች ጥናት ላይ ነው። በአለማችን ረጅም እድሜ ያስቆጠረው አለት 4.0 ቢሊዮን አመት ነው። እነዚህ የሳይንስ ሊቃውንት የይገባኛል ጥያቄዎች ትክክል ላይሆኑ ይችላሉ እና እንደ ንድፈ ሃሳብ የተከፋፈሉ እና በሁሉም ምሁራን የተስማሙበት እውነታ ወይም የአጽናፈ ሰማይ ህግ ላይሆኑ ይችላሉ። የመሬትን ታሪክ በመሬት ጥናት ወይም ጂኦሎጂ በተለያዩ ዘመናት ወይም በእንግሊዝኛው ኢራ ከፋፍሎ ማየት ይቻላል። ይህም ሁሉ የሚታሰበው ከሳይንሳዊ ሊቃውንት ሃልዮ ምርመራ ዘንድ ነው። እነዚህ ዘመናት በቢሊዮን እና ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አመታት እድሜ ያላቸው ሲሆኑ በተለያዩ አነስተኛ ዘመናት ወይም ፔሬድስ ይከፋፈላሉ። ጂኦሎጂ የመሬትን ታሪክ በአራት ዋና ዘመናት ወይም ኢራስ ከፍሎ ያያል። እነዚህም፦ የመጀመሪያው ዘመን ወይም በእንግሊዝኛው ቅድመ ዘመን ወይም በእንግሊዝኛው መካከለኛው ዘመን ወይም በእንግሊዝኛው እና አሁን ያለንበት ዘመን ወይም በእንግሊዝኛው ናቸው። የመጀመሪያው ዘመን ወይም በእንግሊዝኛው አንዳንድ ሳይንቲስቶች እንደሚሉት የምድርን ዕድሜ እና የጊዜ ወቅቶች በንድፈ ሃሳብ ያቀረቡት: ይህ ዘመን ከ4500 ሚሊዮን አመታት በፊት ያለው የመሬት እድሜ ነው። የመሬትን ሰባት ስምንተኛ እድሜ የሚያጠቃልል ነው። ነገር ግን ስለዚህ ዘመን ዘመናዊው ሳይንስ ማወቅ የቻለው ጥቂት ነገር ብቻ ነው። በዚህ ዘመን ህይወት ያለው ነገር ለመፈጠሩ የተገኙ መረጃዎች አነስተኛ ቢሆኑም በምዕራብ አውስትራሊያ 3.46 ቢሊዮን አመታት ያስቆጠረ ህዋስ ወይም ባክቴሪያ ተገኝቷል። ቅድመ ዘመን ወይም በእንግሊዝኛው ይህ ዘመን የሚሸፍነው ከ 542 ሚሊዮን እስከ 251 ሚሊዮን አመታት በፊት ያለውን የመሬት እድሜ ነው። የተለያዩ የዓሳ ዝርያዎችን ጨምሮ ትላልቅ የእንሽላሊት ዘሮች ወይም ዳይኖሰሮች በዘመኑ መገባደጃ አካባቢ ተከስተዋል። መካከለኛው ዘመን ወይም በእንግሊዝኛው ከ251 ሚሊዮን አመት እስከ 65.5 ሚሊዮን አመት በፊት ያለው ጊዜ በዚህ ዘመን የሚጠቃለል ነው። አሁን ያለንበት ዘመን ወይም በእንግሊዝኛው ከ65.5 ሚሊዮን አመታት በፊት ጀምሮ አሁን እስካለንበት ያለውን ጊዜ የሚሸፍነው ይህ ዘመን አብዛሃኛው የመሬት ለውጦች ተከናውነውበታል። የመሬት ከባቢ አየር የመሬት የከባቢ አየር በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ይዘቶች ነበሩት። በውስጡ የሚገኙት ህይወት ላላችው ነገሮች አስፈላጊ የሆኑ ነገርችም ( የኦዞን ንጣፍን ጨምሮ) በየጊዜው ተለዋውዋል።ከባቢ አየራችን በውስጡ 78 በመቶ ናይትሮጅን፣ 21 በመቶ ኦክስጅን፣ 0.93 በመቶ አርገን፣ 0.038 በመቶ ካርቦን ክልቶኦክሳይድ የተባሉ ንጥረ ነገሮችን (ጋዞችን) በውስጡ ይዟል። አሁን ያለው ሁኔታ መሬት ለተጨማሪ 1.5 ቢሊዮን አመታት ህይወት ያላቸው ነገሮች እንዲኖሩባት ያስችላል ተብሎ ይታመናል። ቋጥኛዊ ይዘት ያላቸው ፕላኔቶች የውጭ ማያያዣዎች |ዩ ኤስ ጂ ኤስ የጂኦማግኔቲዝም ፕሮግራም |በናሳ የመሬት ቅኝት |የአየር ንብረት ለውጥ የመሬትን ቅርፅ ለውጦታል - ናሳ |የመሬት ልዩ ልዩ ጠፈራዊ ምሥሎች መልክዐ ምድር ሥነ ፈለክ የመሬት ጥናት
38135
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B5%E1%8A%AE%E1%89%B5%E1%88%8B%E1%8A%95%E1%8B%B5
ስኮትላንድ
ስኮትላንድ (ስኮትላንድ፡ ስኮትላንድ፣ ስኮትላንዳዊ ጋሊክ፡ አልባ የዩናይትድ ኪንግደም አካል የሆነች ሀገር ነች። ከታላቋ ብሪታንያ ደሴት ሰሜናዊ ሶስተኛ ክፍልን የምትሸፍን ዋና ላንድ ስኮትላንድ በደቡብ ምስራቅ በኩል 96 ማይል (154 ኪሎ ሜትር) ድንበር አላት። እና በሌላ መልኩ በሰሜን እና በምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ፣ በሰሜን ባህር በሰሜን ምስራቅ እና በአይሪሽ ባህር በደቡብ የተከበበች ናት ።አገሪቷ ከ 790 በላይ ደሴቶችን ያቀፈች ሲሆን በተለይም በሄብሪድስ እና በሰሜናዊ ደሴቶች ደሴቶች ውስጥ ይገኛሉ ። ዋና ከተማዋን ኤዲንብራን ጨምሮ የህዝቡ ብዛት በሴንትራል ቤልት - በስኮትላንድ ደጋማ ቦታዎች እና በደቡባዊ አፕላንድ መካከል ያለው ሜዳ - በስኮትላንድ ቆላማ አካባቢዎች። ስኮትላንድ በ 32 የአስተዳደር ንዑስ ክፍሎች ወይም የአካባቢ ባለስልጣናት የተከፋፈለ ነው, የካውንስል አካባቢዎች በመባል ይታወቃሉ. ግላስጎው ከተማ በሕዝብ ብዛት ትልቁ የምክር ቤት አካባቢ ሲሆን ሃይላንድ በአካባቢው ትልቁ ነው። እንደ ትምህርት፣ ማህበራዊ አገልግሎቶች እና መንገዶች እና መጓጓዣ ያሉ ጉዳዮችን የሚሸፍን የተገደበ ራስን በራስ የማስተዳደር ስልጣን ከስኮትላንድ መንግስት ወደ እያንዳንዱ ንዑስ ክፍል ተወስዷል። ስኮትላንድ በዩናይትድ ኪንግደም ሁለተኛዋ ትልቅ ሀገር ነች እና በ 2012 ከህዝቡ 8.3% ይሸፍናል ። የስኮትላንድ መንግሥት በ9ኛው ክፍለ ዘመን ራሱን የቻለ ሉዓላዊ አገር ሆኖ እስከ 1707 ድረስ ኖረ። በ1603 የስኮትላንድ ጄምስ ስድስተኛ በውርስ የእንግሊዝና የአየርላንድ ንጉሥ ሆነ፣ በዚህም የሶስቱ መንግሥታት ግላዊ አንድነት ፈጠረ። በመቀጠል ስኮትላንድ በግንቦት 1 ቀን 1707 ከእንግሊዝ መንግሥት ጋር የፖለቲካ ህብረት ፈጠረች አዲስ የታላቋ ብሪታንያ ግዛት። ህብረቱ የስኮትላንድ ፓርላማ እና የእንግሊዝ ፓርላማን የተከተለውን የታላቋ ብሪታንያ ፓርላማ ፈጠረ። እ.ኤ.አ. በ 1801 የታላቋ ብሪታንያ መንግሥት ከአየርላንድ መንግሥት ጋር የፖለቲካ ህብረት ፈጠረ (እ.ኤ.አ.) የታላቋ ብሪታንያ እና የሰሜን አየርላንድ ዩናይትድ ኪንግደም በ 1927)። በስኮትላንድ ውስጥ፣ የዩናይትድ ኪንግደም ንጉሳዊ አገዛዝ ለቅድመ-ህብረት የስኮትላንድ መንግሥት ልዩ ልዩ ዘይቤዎችን፣ ማዕረጎችን እና ሌሎች የግዛት ምልክቶችን መጠቀሙን ቀጥሏል። በስኮትላንድ ውስጥ ያለው የህግ ስርዓት ከእንግሊዝ እና ከዌልስ እና ከሰሜን አየርላንድ የተለየ ሆኖ ቆይቷል። ስኮትላንድ በሁለቱም በህዝብ እና በግል ህግ ውስጥ የተለየ ስልጣንን ይመሰርታል። ከ 1707 እንግሊዝ ጋር ህብረትን ከተቀላቀለበት ጊዜ ጀምሮ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ካሉት የህግ ፣ የትምህርት ፣ የሃይማኖት እና ሌሎች ተቋማት ህልውና መቀጠል ለስኮትላንድ ባህል እና ብሄራዊ ማንነት ቀጣይነት አስተዋጽኦ አድርጓል ። እ.ኤ.አ. በ 1999 ፣ የስኮትላንድ ፓርላማ እንደገና ተቋቁሟል ፣ በብዙ የሀገር ውስጥ ፖሊሲዎች ላይ ስልጣን ያለው 129 አባላትን ባካተተ ፣ ከስልጣን የተወከለ የፓርላማ አባል። የስኮትላንድ መንግሥት መሪ በስኮትላንድ ምክትል የመጀመሪያ ሚኒስትር የሚደገፈው የስኮትላንድ የመጀመሪያ ሚኒስትር ነው። ስኮትላንድ በዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ በ59 የፓርላማ አባላት ተወክላለች። ስኮትላንድ የብሪቲሽ-አይሪሽ ካውንስል አባል ነች፣ አምስት የስኮትላንድ ፓርላማ አባላትን ወደ ብሪቲሽ-አይሪሽ ፓርላማ ምክር ቤት በመላክ እንዲሁም በመጀመሪያው ሚኒስትር የተወከለው የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚቴ አካል በመሆን። ሥርወ ቃል ስኮትላንድ የመጣው ከስኮቲ ነው፣ የላቲን የጌልስ ስም ነው። ፊሊፕ ፍሪማን በግሪክ ስኮቶስ () ትይዩ የሆነውን "ጨለማ፣ ጨለማ" የሚለውን በመጥቀስ፣ ከህንድ-አውሮፓዊ ሥር * ስኮት የተሰኘ የወራሪ ቡድን ስም የመውሰድ እድልን ገምቷል። የኋለኛው የላቲን ቃል ስኮሺያ (“የጋልስ ምድር”) በመጀመሪያ አየርላንድን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሎ ነበር፣ በተመሳሳይም በጥንታዊ እንግሊዝ ስኮትላንድ ለአየርላንድ ጥቅም ላይ ውሏል። በመጨረሻው በ11ኛው ክፍለ ዘመን፣ ስኮትያ ከአልባኒያ ወይም ከአልባኒ ጎን ለጎን ከወንዙ ፎርዝ በስተሰሜን (ግዕላዊ ተናጋሪ) ስኮትላንድን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል። አሁን ስኮትላንድ የሚባለውን ሁሉ ለማካተት ስኮትላንድ እና ስኮትላንድ የሚሉትን ቃላት መጠቀም በመካከለኛው ዘመን መጨረሻ የተለመደ ሆ የጥንት ታሪክ ስለ ስኮትላንድ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጻፈው በ320 ዓክልበ. በግሪካዊው መርከበኛ ፒቲያስ ነበር፣ እሱም የብሪታንያ ሰሜናዊ ጫፍ "ኦርካስ" ሲል የጠራው የኦርክኒ ደሴቶች ስም ምንጭ ነው። የአመራር ሞዴል፣ የሰፈራ መጠናከር የሀብት ክምችት እና የተትረፈረፈ ምግብ ከመሬት በታች እንዲከማች አድርጓል።፡- 11 የሮማውያን የብሪታንያ ድል ፈጽሞ አልተጠናቀቀም, እና አብዛኛው ዘመናዊ ስኮትላንድ በሮማውያን የፖለቲካ ቁጥጥር ስር አልነበሩም. የመጀመሪያው የሮማውያን ወረራ ወደ ስኮትላንድ በ79 ዓ.ም. አግሪኮላ ስኮትላንድን በወረረ ጊዜ; እ.ኤ.አ. ወደ ደቡብ አፕላንድ. በ 1 ኛው ክፍለ ዘመን የተመሰረቱ የሮማውያን ምሽጎች ቅሪቶች በሰሜን በኩል እስከ ሞራይ ፈርት ድረስ ይገኛሉ። በሮማ ንጉሠ ነገሥት ትራጃን (አር. 98–117) የግዛት ዘመን የሮማውያን ቁጥጥር በታይን ወንዝ እና በሶልዌይ ፈርት መካከል ካለው መስመር በስተደቡብ ወደ ብሪታንያ አልፏል። በዚህ መስመር ላይ የትራጃን ተከታይ ሃድሪያን (አር. 117–138) በሰሜን እንግሊዝ የሃድሪያን ግንብ አቆመ፡ 12 እና ሊምስ ብሪታኒከስ የሮማ ግዛት ሰሜናዊ ድንበር ሆነ። የሮማውያን ተጽእኖ በደቡባዊው የአገሪቱ ክፍል ላይ ከፍተኛ ነበር, እናም ክርስትናን ወደ ስኮትላንድ አስተዋውቀዋል: 13-14 : 38 የአንቶኒን ግንብ የተገነባው ከ142 ጀምሮ በሃድሪያን ተከታይ አንቶኒኑስ ፒዩስ (አር. 138–161) ትእዛዝ ሲሆን የሮማን የስኮትላንድ ክፍል ከደሴቱ የማይተዳደር ክፍል በመከላከል በፈርት ኦፍ ክላይድ እና በፈርት ኦፍ ፈርት መካከል ካለው መስመር በስተሰሜን ይገኛል። ወደ ፊት። እ.ኤ.አ. 208-210 በካሌዶኒያ የተሳካ የሮማውያን ወረራ የተካሄደው በ197 በካሌዶኒያውያን የተደረገውን ስምምነት ለማፍረስ በንጉሠ ነገሥት ሰቨራን ሥርወ መንግሥት ንጉሠ ነገሥት ነበር ፣ ግን በታላቋ ብሪታንያ ላይ ዘላቂ ወረራ የተካሄደው በታላቁ ንጉሠ ነገሥት ሴፕቲዩስ ሞት ምክንያት ነው። ሰቬረስ (አር. 193–211) በኤቦራኩም (ዮርክ) ዘመቻ ላይ እያለ እና ካሌዶናውያን በ210–211 እንደገና አመጹ። በሴቨራን ዘመቻ የሮማውያን ጦር ያቆሙት ምሽጎች በአግሪኮላ በተቋቋመው አቅራቢያ ተቀምጠዋል እና በሃይላንድ ውስጥ በግሌን አፍ ላይ ተሰብስበዋል ። ለሮማውያን ታሪክ ጸሐፊዎች ታሲተስ እና ካሲየስ ዲዮ፣ የስኮትላንድ ደጋማ ቦታዎች እና ከወንዝ ፎርዝ በስተሰሜን ያለው አካባቢ ካሌዶኒያ ተብሎ ይጠራ ነበር። ካሲየስ ዲዮ እንዳለው የካሌዶኒያ ነዋሪዎች ካሌዶኒያውያን እና ማኤታኢዎች ነበሩ። ሌሎች ጥንታዊ ደራሲያን "ካሌዶኒያን" የሚለውን ቅጽል በሰሜንም ሆነ በብሪታኒያ ውስጥ የትኛውም ቦታ ላይ ለማመልከት ተጠቅመውበታል, ብዙውን ጊዜ የክልሉን ሰዎች እና እንስሳት, ቀዝቃዛ የአየር ጠባይዋን, ዕንቁዋን እና ታዋቂ የእንጨት ኮረብታዎችን (ላቲን: ጨዋማ) ይጠቅሳሉ, ይህም 2 ኛ- ክፍለ ዘመን ዓ.ም ሮማዊው ፈላስፋ ቶለሚ፣ በጂኦግራፊው፣ ከ ደቡብ-ምዕራብ እንደሆነ ገልጿል። ካሌዶኒያ የሚለው ስም በደንከልድ፣ ሮሃሊየን እና ሺሃሊየን የቦታ ስሞች ላይ ተስተጋብቷል። ስኮቲዎች የተሳተፉበት በብሪታንያ በ4ኛው ክፍለ ዘመን በሮማውያን አገዛዝ ላይ የተካሄደው ታላቅ ሴራ በመጪው ቴዎዶስዮስ ተሸንፏል። በስኮትላንድ ውስጥ ሊሆን የሚችለው ከገዢው ንጉሠ ነገሥት ቫለንስ (አር. 364-378) በኋላ ቫለንቲያ የሚባል አዲስ ግዛት መመስረት አስከትሏል። የሮማውያን ወታደራዊ መንግስት በ 5 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ከደሴቱ ሙሉ በሙሉ ተወግዷል, በዚህም ምክንያት የብሪታንያ አንግሎ-ሳክሰን ሰፈራ እና ሳክሶኖች ወደ ደቡብ ስኮትላንድ እና የተቀረው የምስራቅ ታላቋ ብሪታንያ ፍልሰት ምክንያት ሆኗል. መካከለኛ እድሜ ከስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ፣ አሁን ስኮትላንድ የሚባለው አካባቢ በሦስት አካባቢዎች ተከፈለ፡- ፒክትላንድ፣ በማዕከላዊ ስኮትላንድ ውስጥ የትንንሽ ጌትነት ሥምሪት ሥራ፤፡ 25–26 ደቡብ ምሥራቅ ስኮትላንድን የገዛው የኖርተምብሪያ አንግሎ ሳክሰን መንግሥት፤፡ 18– 20 እና ዳል ሪያታ፣ በአየርላንድ ሰፋሪዎች የተመሰረቱት፣ የጌሊክ ቋንቋንና ባህልን ይዘው ይመጡ ነበር። . ሥዕሎቹ እስከ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ባሪያዎችን ያቆዩ ነበር (በአብዛኛው በጦርነት የተያዙ)።፡ 26–27 በ እና ላይ የጌሊክ ተጽእኖ ሚስዮናውያን ሆነው በሚሰሩት ብዛት ባላቸው የጌሊክ ተናጋሪ ቀሳውስት አመቻችቷል።፡ 23–24 በስድስተኛው ክፍለ ዘመን በአዮና ደሴት ሲሰራ፣ ሴንት ኮሎምባ ከመጀመሪያዎቹ እና በጣም ታዋቂዎቹ ሚስዮናውያን አንዱ ነበር። 39 ቫይኪንጎች ስኮትላንድን መውረር የጀመሩት በስምንተኛው ክፍለ ዘመን ነው። ዘራፊዎቹ ባሪያዎችን እና የቅንጦት ዕቃዎችን ቢፈልጉም ዋናው ተነሳሽነታቸው መሬት ለማግኘት ነበር። በጣም ጥንታዊዎቹ የኖርስ ሰፈሮች በሰሜናዊ ምዕራብ ስኮትላንድ ውስጥ ነበሩ, ነገር ግን በመጨረሻ በባህር ዳርቻ ላይ ብዙ ቦታዎችን አሸንፈዋል. የድሮው ኖርስ በሰሜናዊ ደሴቶች ውስጥ ጋሊክን ሙሉ በሙሉ ተፈናቅሏል፡ 29–30 በዘጠነኛው ክፍለ ዘመን የኖርስ ስጋት ሲናድ ማክ አይልፒን (ኬኔዝ 1) የሚባል ጌኤል በፒክትላንድ ላይ ስልጣን እንዲይዝ ፈቀደለት፣ የዘመናችን ነገሥታት የዘር ሐረጋቸውን የሚከተሉበት ንጉሣዊ ሥርወ መንግሥት አቋቋመ፣ እና የፒክቲሽ ባሕል መጨረሻ መጀመሪያ ላይ ምልክት ያደርጋል። 31–32 አልባ የሚባለው የሲናኤድ መንግሥት እና ዘሮቹ በባህሪው ጌሊካዊ ነበሩ ነገር ግን ከፒክትላንድ ጋር በተመሳሳይ አካባቢ ነበር። በአሥረኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ፣ የፒክቲሽ ቋንቋ ተናጋሪዎቹ ወደ ጋሊሊክ ሲቀየሩ ጠፋ።፡ 32–33 ከምሥራቃዊ ስኮትላንድ ከወንዙ ፎርዝ በስተሰሜን እና ከወንዙ ስፓይ ወንዝ በስተደቡብ፣ መንግሥቱ በመጀመሪያ ወደ ደቡብ፣ ወደ የቀድሞ የሰሜንምብሪያን መሬቶች፣ እና በሰሜን በኩል ወደ ሞራይ።፡ 34–35 በሚሌኒየሙ መባቻ አካባቢ፣ በግብርና መሬቶች ላይ ማእከላዊነት ተፈጠረ እና የመጀመሪያዎቹ ከተሞች መመስረት ጀመሩ፡ 36–37 በአስራ ሁለተኛው እና አስራ ሶስተኛው ክፍለ ዘመን አብዛኛው የስኮትላንድ ግዛት በአንድ ገዥ ቁጥጥር ስር ነበር። መጀመሪያ ላይ የጌሊክ ባህል የበላይ ነበር፣ ነገር ግን ከፈረንሳይ፣ እንግሊዝ እና ፍላንደርዝ የመጡ ስደተኞች የበለጠ የተለያየ ማህበረሰብ ፈጥረዋል፣ የጌሊክ ቋንቋ በስኮቶች መተካት ጀመረ። ባጠቃላይ የዘመኑ ብሔር-አገር ከዚህ ወጣ። በዚህ ጊዜ መጨረሻ ላይ ከእንግሊዝ ጋር የተደረገ ጦርነት የስኮትላንድ ብሔራዊ ንቃተ ህሊና እድገት ጀመረ።፡ 37-39 : 1 ዴቪድ 1ኛ እና ተተኪዎቹ የንጉሣዊ ኃይልን ያማከለ፡ 41-42 እና ዩናይትድ ዋና ስኮትላንድን በመቆጣጠር ክልሎችን ያዙ። እንደ ሞራይ፣ ጋሎዋይ እና ካትነስ በ1164 የሶመርሌድ ሞትን ተከትሎ በተለያዩ የስኮትላንድ ጎሳዎች ሲገዙ በነበሩት ሄብሪዶች ላይ ስልጣኑን ማራዘም ባይሳካለትም። ሁለቱም የአንግሎ-ኖርማን ገቢ ፈጣሪዎች እና ተወላጆች የጌሊክ አለቆች ንጉሱን በማገልገል ምትክ መሬት ተሰጥቷቸዋል።፡ 53–54 በዚህ ጊዜ ውስጥ ከስኮትላንድ ደቡብ ጎረቤት ጋር ያለው ውስብስብ ግንኙነት የስኮትላንድ ነገሥታት የእንግሊዝ የፖለቲካ አለመረጋጋትን ለመበዝበዝ የተሳካ እና ያልተሳካ ሙከራ በማድረግ ይታወቃል። በመካከለኛው ዘመን በስኮትላንድ እና በእንግሊዝ መካከል ረዥሙ የሰላም ጊዜ፡ ከ1217-1296
52066
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%8B%8D%E1%8A%95%20%E1%8A%90%E1%89%A5%E1%8B%A9%20%E1%88%98%E1%88%80%E1%88%98%E1%8B%B5%20%E1%88%80%E1%88%B0%E1%89%B0%E1%8A%9B%20%E1%8A%93%E1%89%B8%E1%8B%8D%3F
እውን ነብዩ መሀመድ ሀሰተኛ ናቸው?
ቢስሚላህ አልሀምዱሊላህ እውን ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ሀሰተኛ ነብይ ናቸው? ሀሰተኞች አላማቸው አለማዊ ጥቅም ማግኘት ነው ማለትም ለስልጣን፣ ለክብር፣ ለዝና፣ለገንዘብ፣ለሴት.... ብለው ነው ነብይ ሳይሆኑ ነብይ ነኝ ሚሉት። ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች አብዛኞቹ ሚያስቡት ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ነብይ ነኝ ሲሉ ሁሉም ሰው ባንዴ ነብይነታቸውን ተቀብሎ ያመናቸው እና የተከተላቸው አርገው ነው ሚያስቡት። ነገሩ ግን በተገላቢጦሽ ነው የሆነው። ከነብይነታቸው በፊት ታማኙ ሙሀመድ በተባሉበት ምላስ አላህ ነብይ አድርጎ ልኮኛል ሲሉ ተስተባብለዋለ፣ ውሸታም፣ መተተኛ፣ ደጋሚ፣ እብድ.... ተብለዋል። ፊታቸው ላይ ተተፍቶባቸዋል ለፈጣሪ በመስገድላይ እያሉ ፈርስ ተደፍቶባቸዋል እየሱስ መከራን እንደተቀበለው ሁላ ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ያልደረሰባቸው የመከራ አይነት የለም ያውም በወገኖቻቸው ተሰድበዋል ፣ተደብድበዋል ፣በድንጋይ ተወግረዋል ፣መአቀብ ተጥሎባቸዋል፣የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸዋል ፣ከሀገራቸው ተባረዋል የተጣለባቸው መአቀብ ለሶስት ዓመታት የቆየ ሲሆን ማንም ሰው ከነብዩ ሙሀመድ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገበያየት በጋብቻ መተሳሰር ማናገር ቤታቸው መግባት የሚከለክል ነበር። አስባችሁታል መተዳደሪያው ንግድ ብቻ ለሆነ ማህበረሰብ ለሶስት ዓመታት መሸጥ መለወጥ ሲከለከል ኑሮ እንዴት እንደሚከብድ። ሚላስ ሚቀመስ አጥተው እንዴት እንደተቸገሩ ። የመካ ባላባቶች ለ ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ሙሀመድ ሆይ ክብር ፈልገክ ከሆነ የሁላችንም አለቃ እናድርግህ ያላንተ ፈቃድ ምንም አንፈፅምም ንግስናም ፈልገክ ከሆነ ንጉስ አድርገን እንሹምህ ሀብትም ከሆነ ምትፈልገው ያሻህን ያህል ሀብት እንስጥህ ሴትም ፈልገክ ከሆነ ቆነጃጅትን መርጠን እንዳርልህ ታመክም ከሆነ አለ የተባለ ሀኪም አስመጥተን እናሳክምህ(ሀኪሙ ይፈውስህ) አንተ ብቻ #"አላህ ነብይ አድርጎ ልኮኛል አላህን ብቻ አምልኩ ጣዖታትን ራቁ" ምትለውን ተው ብለው መደራደሪያ አቅርበውላቸው ነበር በዚ ግዜ የነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ)መልስ ፀሀይን በቀኝ እጄ ጨረቃን በግራ እጄ ላይ ብታስቀምጡልኝ እንኳን አላህ የላከኝን መልእክት ለሰው ዘር እስከማደርስ ወይም እስከምሞት ድረስ አላርፍም ብለው ነበር የመለሱት። ታዲያ ሀሰተኛ ነብይ ቢሆኑ ኖሮ ይህን ሁሉ አለማዊ ጥቅም እምቢ ብለው ያን ሁሉ መከራ ይሸከሙ ነበር ? መልሱን ለናንተው ትቸዋለው ሌላም ማባበያ አቅርበውላቸው ነበር እሱም አንተም የኛን ጣዖቶች አምልክ እኛም ያንተን አምላክ እናምልክ መሀል ላይ እንገናኛለን ብለዋቸው ነበር የነብዩ መልስ ለኔም የራሴ እምነት አለኝ ለናንተም የራሳችሁ እምነት አላችሁ የፈለገ ሰው ያሻውን እምነት ይከተል የእምነት ነፃነት ይኑር ብለው ነው የመለሱላቸው። እየሱስም የሀገሩ ሰዎች ከማመን ሲሰናከሉበት ማርቆስ 6 :4 ኢየሱስም፣ “ነቢይ የማይከበረው በገዛ አገሩ፣ በዘመዶቹ መካከልና በቤተ ሰቡ ዘንድ ብቻ ነው” ነብዩ ሙሀመድም (ሰ.ዐ.ወ) የገዛ ዘመዶቻቸው እና የሀገራቸው(የመካ) ሰዎች አናምንህም ብለው አስተባብሏቸው ከዚህም አልፈው ሊገድሏቸው ሲሉ በመጨረሻ ተወልደው ያደጉባትን መካን ትተው ወደ መዲና ተሰደዱ የመዲና ነዋሪኦች በመልካም ተቀበሏቸው እዛ አዲስ መሀበረሠብ ማነፅ ጀመሩ ። ኢሄኔ መካውያን መዲና ላይ የንግድ መአቀብ ጣሉባት ይህም ሳይበቃ ጦርነት አወጁባቸው። ይህ ሁሉ መከራ ነብይ በመሆናቸው ነው። እየሱስም የተሰቃየው በዚው ምክንያት ነው። ብዙ ሚስቶች ማግባታቸው አላማው የሴት ፍላጎት ቢሆን ኖሮ ልጃገረድ የሆኑትን ብቻ ነበር ሚሰበስቡት። ነገር ግን ከአጠቃላይ ሚስቶቻቸው አንዷ ብቻ ናት ልጃገረድ ሌሎቹ አግብተው የፈቱ ባሎቻቸው የሞቱባቸው እድሜያቸው የገፋ ሴቶች ናቸው። አላማው በዘመኑ ከአንድ ጎሳ አባል ጋር በጋብቻ ከተሳሰርክ በአማችነት የተነሳ ያጎሳ ከአንተ ጋር ሰላም ይፈጥራል ከጎንህ ይቆማል ጦርነት አያውጅብህም ። በሌላ ቋንቋ ለሰላም ሲባል ማለት ነው። ለዚህ እና ሌሎች ምክንያቶች በርካታ ሚስቶችን አግብተዋል። ይህ ባይሆንማ ኖሮ በርካታ ኮረዶችን ብቻ ባገቡ ነበር ። ሁሉም በሚያሰኝ መልኩ የሀገሪቱ ሴቶች (ልጃገረዶች) የነብዩ ሚስት መሆንን ይመኙ ነበር። ምክንያቱም ፦ ጀግና፣ ቆንጆ፣ የሀገር መሪ፣ የጥሩ ስነ-ምግባር ባለቤት በዚህ ላይ ተወዳጅ ነብይ ነበሩና ነው። የኛ ከሆነ ከሰል ነጭ ነው ቢልህም ትክክል ነው የነሱ ከሆነ ወተት ነጭ ነው ቢልህም ስተት ነው የሚል አስተሳሰብ አግባብ አይደለም የነገሩንን ብቻ አምኖ መቀበል ሳያሆን እውነቱን ለማወቅ ሁሉንም እውነተነኛ መፅሀፍት በሚዛናዊ አእምሮ በማንበብ አመዛዝኖ እውነታው ላይ መድረስ ነው ያለብን። እየሱስ ነጣቂ የሆኑ ሀሰተኛ ነብዮች እና ሀሰተኛ ክርስቶሶች እንደሚነሱ መናገሩ እንዲሁም እንዳያስቷችሁ ማለቱ እውነት ነው፡፡ ነብዩ ሙሀመድም(ሰ.ዐ.ወ) ሀሰተኛ ነብዮች እደሚነሱ ተናግረዋል #አላህ ከኔ በፊት ብዙ ነብያትን ልኳል እኔ የመጨረሻው ነብይ ነኝ ከኔ ቡሀላ ነብይ አይላክም ነገር ግን ሀሰተኞች ነብይ ነኝ ብለው የሚሉ ሰዎች ይነሳሉ ሀሰተኞች ናቸው እንዳታምኟቸው ብለዋል። ያሉትም አልቀረ ነብዩ ሊሞቱ አቅራቢያ ሁለት ሰዎች ነብይ ነኝ ብለው በተለያዩ ቦታዎች ላይ ተነስተው ነበር አሁንም በየ አዳራሹ ነብይ ነኝ ሚሉ ሀሰተኞች ሞልተዋል። ነብይነት ከፈጣሪ የሚሰጥ እንጂ በህዝብ ድምፅ ወይም ነኝ በማለት የሚገኝ አይደለም። የአላህ ሰላም በነብዩ ሙሀመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ላይ ይሁን። አላህም(ፈጣሪ) እንዲህ ሲል ነብይነታቸውን ገልፇል ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድም ሰው አባት አይደለም፡፡ ግን የአላህ መልክተኛና የነቢዮች መደምደሚያ ነው፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ (ሱረቱ አል- አሕዛብ - 40) እርሱ ያ መልክተኛውን በመሪ መጽሐፍና በእውነተኛ ሃይማኖት በሃይማኖት ሁሉ ላይ ሊያልቀው የላከ ነው፡፡ መስካሪም በአላህ በቃ፡፡ (ሱረቱ አል ፈትሕ - 28) እነዚያ የካዱ ከአላህ መንገድም የከለከሉ (አላህ) ሥራዎቻቸውን አጠፋባቸው፡፡ (ሱረቱ ሙሐመድ - 1) እነዚያም ያመኑ፣ በጎዎችንም የሠሩ፣ በሙሐመድ ላይም የወረደው እርሱ ከጌታቸው ሲኾን እውነት ስለ ኾነ ያመኑ ከእነርሱ ላይ ኃጢአቶቻቸውን ያባብሳል፡፡ ኹኔታቸውንም ሁሉ ያበጃል፡፡ (ሱረቱ ሙሐመድ - 2) ይህ እነዚያ የካዱት ውሸትን የተከተሉ በመኾናቸውና እነዚያም ያመኑት ከጌታቸው የኾነን እውነት ስለተከተሉ ነው፡፡ እንደዚሁ አላህ ለሰዎች ምሳሌዎቻቸውን ያብራራል፡፡ (ሱረቱ ሙሐመድ - 3)
32729
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%86%E1%8D%8B%E1%88%AA%E1%8B%8E%E1%89%B9
ቆፋሪዎቹ
ቆፋሪዎቹ (እንግሊዝኛ፦ /ዲገርዝ/) ከ1641 እስከ 1643 ዓ.ም. ድረስ በእንግሊዝ አገር የቆየ ኅብረተሠባዊ እንቅስቃሴ ነበረ። በ1641 በኦሊቨር ክሮምዌል ዘመን የመሠረተው ሳባኪው ጄራርድ ዊንስታንሊ ሲሆን ደንበኛ ስማቸው «ዕውነተኛ አስተካካዮቹ» (/ትሩ ሌቨለርዝ/) ይባል ነበር። ሆኖም ከድርጊቶቻቸው የተነሣ «ቆፋሪዎቹ» ተብለው ይታወቁ ጀመር። «ዕውነተኛ አስተካካዮቹ» የሚለው ስያሜያቸው የመጣ ከሐዋርያት ሥራ 4፡32 ቃል መሠረት የምጣኔ ሀብታቸው እኩልነት እምነት ስለ ነበራቸው። ቆፋሪዎቹ ርስትን በ«ማስተካከል» የቆየውን ኅብረተሠብ ለማሻሻል ሞከሩ። ዋና ሃሳባቸው በትንንሽ እርሻ ሰፈሮች ላይ በግብርና ሁላቸው እኩል ሆነው ለመኖር ነበር። በዚሁ ዘመን ከተነሡት ከእንግሊዝ ቤተክርስቲያን ተቃራኒ እንቅስቃሴዎች አንዱ ናቸው። 1641 ዓ.ም. በእንግሊዝ አገር ኅብረተሠባዊ ሁከቶች የበዙበት አመት ነበር። የፓርላማ ወገን በጦር ሜዳ ላይ በሰፊው ድል አድርገው ቢሆንም የተሸነፈው ንጉሥ 1ኛ ቻርልስ ገና ስምምነት አልፈቀድም ነበር። በመጨረሻ ፓርላማና ሠራዊቱ እንደ አታላይ ይሙት በቃ ፈረዱበት። የንጉሥ ጉባኤ በአዲስ መንግሥት ጉባኤ ወዲያው ተተካ። የፓርላማም ሥልጣን በጠብ ብዛት ስለ ተደከመ ይህ አዲስ ጉባኤ በሠራዊቱ ተገዛ። ብዙ ሰዎች በፖለቲካ ውስጥ ገብተው የአዲስ መንግሥት ለውጥ እንዴት እንደሚሻሻል ያላቸውን ልዩ ልዩ ሃሣቦቻቸውን እያቀረቡ ነበር። የቀደመውን ንጉሥ ልጅ 2ኛ ቻርልስ በዙፋን ላይ ማስቀመጥ የፈለጉ ወገን ሲኖር እንደ ክሮምዌል የነበሩት መሪዎች ደግሞ ባለ ሃብታሞች ብቻ የሚውከሉበት ፓርላማ ፈለጉ። በጆን ሊልቡርን መጻሕፍት ተጽእኖ የወጣ ተቃራኒ ወገን ደግሞ እያንዳንዱ አዋቂ ወንድ ባላቤት እንዲወከል እንጂ በሀብት መሠረት እንዳይሆን ጣሩ። እነኚህ «አስታካካዮቹ» (/ሌቨለርዝ/) ተባሉ። ከዚህ በላይ «አምስተኛው ንጉዛት ሰዎች» የሚባለው ወገን ሃይምኖታዊ መንግሥት () ፈለጉ። ከነዚህ ወገኖች መካከል የዊንስታንሊ ቆፋሪዎች ሥርነቀል መፍትሔ አራመዱ። ጄራርድ ዊንስታንሊና 14 ሌሎች እራሳቸውን ከአስተካካዮቹ ለመለየት ስማቸውን «ዕውነተኛ አስተካካዮቹ» ብለው አንድ ጽሑፍ አሳተሙ። ሃሳባቸውን ተግባራዊ አድርገው የጋራ መሬት ለማረስ ከጀመሩ በኋላ ሰዎች «ቆፋሪዎች» ይሉዋቸው ነበር። በቆፋሪዎቹ እምነት ተፈጥሮአዊ አኗርኗር አይነተኛ ነበረ። ዊንስታንሊ እንዳለው «ዕውነተኛ ነጻነት ሰው ምግቡንና ደህንነቱን ባገኘበት ይተኛል፣ ያውም በምድሪቱ ጥቅም ነው።» በቆፋሪዎች አስተሳሰብ፣ ከኖርማኖች ወረራ (1058 ዓ.ም.) አስቀድሞ እንግሊዞች ቀና፣ ጻድቅ፣ እና በእኩልነት የኖረ ነገድ ሆነው ነበር። ኖርማኖች ከወረሩ በኋላ ግን መንግሥቱን በመያዛቸው መኳንንት ሆኑ፣ ኗሪ እንግሊዞች ግን ተራ ሕዝቦች ሆነው በኖርማኖች ሥር («የኖርማኖች ቀንበር») ተጨቆኑ። ዊንስታንሊ እንደ መሰለው የእንግሊዝ ንጉሥና የእንግሊዝ መንግሥት የኖርማኖች ተከታዮች ስለ ሆኑ መጣል ነበረባቸው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ኮረብታ፣ ወይብሪጅ፣ ሳሪ በሚያዝያ 1641 ዓ.ም. ለመንግሥት ጉባኤ በቀረበው ደብዳቤ መሠረት፣ ብዙ ግለሠቦች በቅዱስ ጊዮርጊስ ኮረብታ፣ ወይብሪጅ ላይ፣ በኮብሃም፣ ሳሪ ዙሪያ በጋራ መሬት ላይ አትክልትን ይተክሉ ጀመር፣ ይህም የምግብ ዋጋ ካለፈው ጊዜ ይልቅ ከሁሉ ከፍ ባለ ደረጃ ሲደርስ ነበር። የአቶ ሳንደርዝ ደብዳቤ እንዳወራው፣ «ሰው ሁሉ መጥቶ እንዲረዳቸው ሲለምኑ ምግብን፣ መጠትንና ልብስን በምላሽ እንዲያገኙ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።» አጥሮቹን ሁሉ በመፍረስ የዙሪያው ሕዝብ አንድ ላይ እንዲሠሩ ለማድረግ አሰቡ። በ10 ቀን ውስጥ ቁጥራቸው ብዙ ሺህ እንዲሆን አሳመኑ። «ዕቅድ በእጅ እንደ ያዙ የሚል ፍርሃት አለ።» በዚሁም ወር፣ ቆፋሪዎቹ «የእውነተኛ አስተካካዮቹ መርኅ ተራመደ» የሚባል ጽሑፍና አቤቱታ አሳተሙ። በዙሪያው ባለርስቶች ጥያቄ፣ የአዲስ አራያ ሠራዊት አለቃ ሰር ቶማስ ፌይርፋክስ ከወታደሮች ጋር ደረሰና ዊንስታንሊንና ሌላ ቆፋሪ ዊልያም ኤቨራርድን በጥያቄ መረመራቸው። ኤቨራርድ ብርቱ ችግር እንደ ፈላ ስለ መሰለው ከእንቅስቃሰው ቶሎ ወጣ። ዳሩ ግን በፌይርፋክስ አስተያየት ቆፋሪዎች ጉዳት የሚያምጡ ስላልነበሩ፣ ባለርስቶቹ ጉዳዩን በችሎት እንዲቀጥሉት መከረ። ዊንስታንሊ በሰፈሩ ላይ ቆየና ቆፋሪዎቹ ስላገኙት እንቅብቃቤ ለመጻፍ ቀጠለ። የርስቱ ጌታ ፍራንሲስ ድረይክ (ይህ የስመ ጥሩ ተጓዥ ፍራንሲስ ድረይክ አልነበረም) ሆን ብሎ በቅጥ ሊያሳድዳቸው ሞከረ። ወንበዶችን በቡድን አሰብስቦ ብዙ ጊዜ ከመደበደባቸው በላይ አንዴ የጋራ ቤታቸውንም አቃጠሉ። በችሎቱ ጉዳይ ቆፋሪዎች ለራሳቸው እንዳይመሰክሩ ተከለከለ። መረኑ የ«ዘላባጆቹ» (/ራንተርዝ/) ወገን አባላት ተብለው ተፈረደባቸው። (እንዲያውም ግን ዊንስታንሊ የዘላባጆች መሪ ላውረንስ ክላርክሶንን መረንንነትን ስለማስተማሩ ወቀሰው) በችሎቱ ጉዳይ ስለ ተሸነፉ፣ መሬቱን ለመልቀቅ እምቢ ካሉ ሠራዊት በእርግጥ ያስወጣቸው ነበር፤ ስለዚህ ለባለርስቶቹ ደስታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ኮረብታን በነሐሴ 1641 ተዉ። ሊተል ሂስ በኮብሃም፣ ሳሪ ዙሪያ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከተሳደዱት ቆፋሪዎች መካከል አንዳንድ በትንሽ ርቀት ወደ ሊተል ሂስ ፈለሱ። 4.5 ሄክታር የመሬት ስፋት ልክ ታረሰ፤ ስድስት ቤቶች ታሠሩ፣ የበጋ ሰብል ተመረተ፣ አንዳንድ ጽሑፍ ታተመ። መጀመርያ በርኅራኄ ያያቸው የኮብሃም ርስቱ ጌታ ካህን ጆን ፕላት በኋላ ዋና ጠላታቸው ሆነ። በሥልጣኑ አማካይነት የዙሪያው ሕዝብ እንዳይረዳቸው አሰናከለ፤ እንዲሁም ቆፋሪዎቹም ሆነ ንብረታቸው በግፍ እንዲበደሉ አደረገ። በሚያዝያ 1642 ዓ.ም. ፕላትና ሌሎች ባለርስቶች ከርስታቸው በፍጹም አባረሯቸው። ዌሊንግቦሮ፣ ኖርሳምቶንሺር ሌላ የቆፋሪዎች ሰፈር ደግሞ በዌሊንግቦሮ፣ ኖርሳምቶንሺር አካባቢ ቆመ። ይህ ማህበር በ1642 ዓ.ም. ያሳተመው አዋጅ እንዲህ ተባለ፦ «እኛ የዌሊንግቦሮ መንደር በኖርሳምቶን ድኃ ኗሪዎች በይርሻንክ በተባለው በዌሊንግቦሮ ኗሪዎች ጋራ ወና ምድር ላይ ለመቆፈር፣ ለማዳበርና እህልን ለመዝራት ፈቅደን የጀመርንበት መሠረቶችና ምክንያቶች አዋጅ...» ይህ ሠፈር የተጀመረው ከሳሪ ቆፋሪዎች ግንኙነት የተነሣ ይመስላል። በመጋቢት 1642 ከሳሪው ሰፈር የደረሱ 4 ተልእኮዎች በባኪንግሃምሸር ታሠሩ፤ የያዙትም ደብዳቤ በጄራርድ ዊንስታንሊና በሌሎች ቆፋሪዎች ተፈርሞ ሰዎች በየቦታው ለራሳቸው የቆፋሪ ሠፈር ለማቆምና የሳሪን ሰፈር በስንቅ ለመርዳት የሚል ልማኔ ነበር። «ፍጹም በየዕለቱ» የሚባለው ጋዜጣ እንደሚናግረው፣ እነኚህ ተልእኮዎች ከሳሪ ወደ ሚድልሴክስ፣ ህርትፎርድሺር፣ ቤድፎርድሸር፣ ባኪንግሃምሸር፣ ባርክሸር፣ ሃንቲንግደንሸር እና ኖርሳምቶንሸር አውራጃዎች ከተጓዙ በኋላ ታሠሩ። በሚያዝያ 10 ቀን 1642 ዓ.ም. የመንግሥት ጉባኤ የኖርሳምቶንሸር ዳኛ አቶ ፔንትሎው በሚከተለው ችሎት «በአቅራቢያው ባሉት አስተካካዮች ላይ» ክስ እንዲያካሄድባቸው ታዘዘ። የአይቫ ቆፋሪዎች እንደ መዘገቡት፣ ከዌሊንግቦሮ ቆፋሪዎች 9 በወህኒ ታስረው ምንም ወንጀል በነርሱ ማረጋገጥ ባይቻልም ኖሮ ዳኛው ነጻ እንዳያስወጣቸው እምቢ ብለው ነበር። አይቫ፣ ባኪንግሃምሸር ከሳሪና ከኖርሳምቶንሸር ሠፈሮች ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሌላ ቆፋሪዎች ሰፈር በአይቫ፣ ባኪንግሃምሸር ተገኘ። ይህም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ኮረብታ በ14 ኪ.ሜ ይርቃል። የአይቫ ቆፋሪዎች አዋጅ እንዳለው፣ ሌሎችም ሠፈሮች ደግሞ በባርኔት፣ ህርትፎርድሸር፣ በኤንፊልድ፣ ሚድልሴክስ፣ በዳንስተብል፣ ቤድፎርድሸር፣ በቦስዎርስ፣ ግሎስተርሸር እና እንዲሁም በኖቲንግሃምሸር ኖሩ። በተጨማሪ የሳሪ ሰፈር ከተሳደደ በኋላ፣ ቆፋሪዎቹ ልጆቻቸውን በአሳዳጊነት መተው እንደ ተገደዱ ይገልጻል። የእንቅስቃሴው መጨረሻ በመላ እንግሊዝ አገር የቆፋሪ ሰፈሮች በጠቅላላ ከጥቂት መቶ ሰዎች በላይ አልነበሯቸውም። በባለርስቶችና በመንግሥት ጉባኤ ማሳደድ ምክንያት እንቅስቃሴው በ1643 ዓ.ም. ጨረሰ። («ዕውነት ከነውሩ በላይ ራሱን ሲያነሣ» - 1641 ዓ.ም.፤ ጄራርድ ዊንስታንሊ) («የጽድቅ አዲስ ሕግ» - ጥር 1641፣ ጄራርድ ዊንስታንሊ) («የዕውነተኛ አስተካካዮች መርኅ ተራመደ» - ... («በእንግሊዝ አገር ከተጨቆኑት ድኆች ባለርስቶች ለተባሉት ሁሉ የደረሰው አዋጅ» - የአውሮፓ ታሪክ የክርስትና ክፍልፋዮች
48464
https://am.wikipedia.org/wiki/Sahabah%20story%28%E1%88%B6%E1%88%80%E1%89%A3%29/%E1%88%99%E1%88%B5%E1%8B%93%E1%89%A5%20%E1%8A%A2%E1%89%A5%E1%8A%91%20%E1%8A%A1%E1%88%98%E1%8B%AD%E1%88%AD%28%E1%88%A8.%E1%8B%90%29
Sahabah story(ሶሀባ)/ሙስዓብ ኢብኑ ኡመይር(ረ.ዐ)
ሙስዐብ ኢብኑ ዑመይርሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር የህይወት ታሪኩ ለሰው ልጅ ክብር ነው፡፡ የመስዋዕትነትና ፅኑ እምነት ተምሳሌት ነው፡፡ የሙስዓብ ኢብኑ ዑመይር የኢሥላም ጉዞ ……. ዑመይር በባህረ ሰላጤዋ እምብርት መካ፣ የሁሉ ማረፊያ በሆነው በኢብራሂም የተገነባውን ቤት ካዕባን ከበው ከሚኖሩ ከበርቴዎቿ መሃል አንዱ ነው፡፡ ስልጣንና ሀብት ነበረው፡፡ ታዲያ ደስታና ጫወታ በከበባት በአንዷ ለሊት የመካ ከበርቴዎች ሳቅና ፌሽታ ወደሚንጣት ቤት ተፋጠኑ፡፡ ይህ ሁሉ ታዲያ ዑመይርንና ኸናስ ቢንት ማሊክ የተባለችውን ባለቤቱን እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት ነበር፡፡ አላህ አዲስ ልጅ በመስጠት ከችሮታው ዋለላቸው፡፡ ሙስዐብን መልከ መልካሙን፣ ሙሰዐብን የቁረይሽን ህያው ጌጥን…… ወራት ተፈተለኩ፡፡ዓመታት ነጎዱ፡፡ ታዲያ በእያንዳንዱ የህይወቱ እርከኖች ላይ ምቾትና ተድላ አብረውት ነበሩ፡፡ ከወላጆቹ በኩል የእንክብካቤው ብዛት ምንም እስከማይቀር ድረስ ነበር፡፡ በተለይ እናቱ ከሌሎች ከበርቴ ባልንጀሮቿ ልጆች ጎልቶ እንዲታይ ለውጫዊ ገፅታው ከፍተኛ መዋለ-ንዋይ ታፈስ ነበር፡፡ መካ ላይ የወንድ ውበት ሲነሳ ግንባር ቀደሙ ነበር፡፡ ገፅታው ለእይታ ማራኪና ቆንጆ ነበር፡፡ ሙስዐብ በመካ ጎዳናዎችና መንገድ ጠርዞች ካለፈ እርሱን ለማየት የቆነጃጅትና ውበት አድናቂዎች አንገት ይመዘዛል፡፡ ሙስዓብ ሁሌ ደስተኛና ፈገግታ የማይለየው ለጋ ወጣት ነበር፡፡ ከእድሜው ለጋነትና ውብ ገፅታው የተነሳ የስበሰባዎችና ጥሪዎች ጌጥ ነበር፡፡ ውበቱና የአዕምሮው ብስለት የሸፈቱ ልቦችን የተዘጉ በሮችን ይከፍቱ ነበር፡፡ ወራት ጉዟቸውን ቀጥለዋል አመታትም ቅብብሎሹን አጡፈውታል፡፡ የሙስዓብም የህይወት እሽክርክሪት ቀጥሏል፡፡ ህመም፣ጭንቀትና ችግርን ፍጹም አያውቃቸውም፡፡ ነገር ግን የሙስዐብ እናት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሁሌም የጥልቅ አስተሳሰብን ፋና ታያለች፡፡ከብሩህ ፊቱ ላይ ጥንካሬንና ቆራጥነትን ታነባለች፡፡ ቢሆንም ግን የዚህ ጥንካሬ ምንጩ ርቋታል፡፡ እናት የልጇን ውስጥ የማንበብ ችሎታ ቢኖራትም ይህ ግን ተሳናት፡፡ ቀናት ወደፊት አንድ ሲሉ የሙስዓብም ጥንካሬ ይፈረጥማል፡፡ ዛሬ ያለበት ላይ ሆኖ ያለፉ ቀናቱን ሲያስባቸው አሰልቺ ህልሞችና ቅዠት ሆኑበት፡፡ ከእለታት በአንዱ ቀን ይህ ወጣት ሰዎች ከታማኙ ሙሃመድ ሰምተው የሚያወሩትን ይሰማል፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) አላህ እርሳቸውን አብሳሪና አስጠንቃቂ አድርጎ እንደላካቸው፣ ወደ ብቸኛው ተመላኪ አንድነት ተጣሪ እንደሆኑ ይናገራሉ፡፡ መካ ከተማ ነግቶ በመሸ ቁጥር ጭንቀትና ጉዳይዋ ሙሐመድና ኢስላም ከሆኑ ሰንብቷል፡፡ ታዲያ ይህ በምቾት ክልል ውስጥ ያለው መልካሙ ሙስዓብ የዚህን ወሬ ዱካ ከሌሎች በተለየ መልኩ አፈንፍኖ ነበር የሚሰማው፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ካመኑ ተከታዮቻቸው ጋር በመሆን ከቁረይሽ ረብሻና ማደናቆር ራቅ ብለው ሶፋ ተራራ ስር በሚገኘው አርቀም ቤት ውስጥ እንደሚሠበሠቡ ሠማ፡፡ አላቅማማም፡፡ የማየትና እርጋታ ናፍቆት እየቀደመው ወደ አርቀም ቤት አመራ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ለባልደረቦቻቸው ቁርአንን ያነቡላቸዋል፡፡ ቀጥሎም ለታላቁ አላህ ይሰግዳሉ፡፡ ኢማን በሙስዓብ ልብ ውስጥ ቦታውን ሲይዝ አልቆየም፡፡ ከነብዩ(ሰዐወ) ልቦና ተንቆርቁሮ በከናፍሮቻቸው መሃል የሚወጣው የቁርአን ብርሃናማ መልዕክት ወደሚሰሙ ጆሮዎችና ወደሚያስተነትኑ ህሊናዎች ይፈሳሉ፡፡ በዚህች ምሽት ታዲያ የሙስዓብ ልቦና ተረታ፡፡ አንዳች ነገር ከቆመበት ቦታ ፍንቅል አደረገው፡፡ ያላሰበው የደስታ ስሜት ሊያበረው ቀረበ፡፡ ድንገት ነብዩ(ሰዐወ) ዘንድ ተጠጋ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ)በቀኝ እጃቸው የሙስዓብን ደረት ዳበሱት፡፡ እርግጥ የርሱ እርጋታ ጥልቅ ነበር፡፡ በዓይን እርግብግብታ ቅፅበት የጥበብን ጥግ ከዕድሜው በላይ ተላበሰ፡፡ የዘመናትን የጉዞ መስመር ሊቀይር ታጨ፡፡ እናት ልጇን በሃሳብ ዱካ ትከተለው ጀመር፡፡ ተፈታተነችውም፡፡ ልጅ ግን እርጋታው ይጨምራል፡፡ ዑስማን ኢብኑ ጦልሐ አል ሂንዲ ለእናቱ ኢስላምን እንደተቀበለ ሲነግራት ብዙም አልቆየም፡፡ በእርግጥ ዑስማን ሙስዓብ የነብዩን(ሰዐወ) ዓይነት ስግደት ሲሰግድ አይቶት ነበር፡፡ ሙስዓብ ጥቅልል ብሎ ዳሩል አርቀም(ነብዩ መካ ውስጥ ኢስላምን በድብቅ ያስተማሩበት የመጀመሪያው ቤት ነው)ገባ፡፡ በኢስላማዊ ጥሪ ታሪክና ህይወት ውስጥ ህያው ቅርስ ወደሆነችው ቤት፡፡ በወቅቱ በሙስሊሞች ጉልበት ላይ ተጨማሪ ኃይል ሆነ፡፡የነብዩ(ሰዐወ) ኢስላማዊ ጥሪ ከደሙ ተዋሃደች፡፡ እምነቱን በማንነቱ ላይ ከታች ወደ ላይ ካበው፡፡ ከማመኑ በፊት የነበረበትን ህሊናዊ ጨለማ የኋሊት ቃኘው፡፡ አሁን ስላለበት ኢስላማዊ ብርሃንና ጠንካራ፣ ነፃ ተከታዮቹ አስተነተነ፡፡ የሙስዓብ ኢስላምን መቀበል ትልቅ ስደት ነበር፡፡ ሙስዓብ የመጀመሪያውን ስደት ያደረገው ከምድራዊ ብልጭልጮችና ጌጧ ወደ አላህና መልዕክተኛው ነበር፡፡ የጥልቅ ለውጡ ሚስጥሩም ይኸው ነበር፡፡ መካ ውስጥ የኢስላም ሕንፃ ግንባታ አንድ ጡብ ለመሆን በቃ፡፡ ሙስዓብ ኢስላምን ከመቀበሉ ጋር ተያይዞ ከእናቱ በስተቀር ምድር ላይ የሚፈራው ኃይል አልነበረም፡፡ የእናቱ ነገር ግን አሳሰበው፡፡ አላህ በጉዳዩ ላይ ፍርዱን እስኪያመጣ ድረስ ኢስላምን መቀበሉን መደበቅ እንዳለበት ወሰነ፡፡ ነገር ግን መካ በዚያ ወቅት ምንም ሚስጥር የላትም፡፡ የቁረይሽ ዓይንና ጆሮ በየመንገዱ ላይ መረጃን ይፈልጋል፣ያሰራጫልም፡፡ በእያንዳንዷ የእግር ፋና ላይ ትንታኔ ይሰጣል፡፡ ሙስዓብ እናቱ፣ ቤተሰቦቹና ቅርብ ዘመዶቹ በሙሉ ኢስላምን እንደተቀበለ አወቁበት፡፡ ነገርግን በመኃላቸው ቆሞ በፅናት ነብዩ(ሰዐወ) የተከታዮቻቸውን ልቦና የሚያፀዱበትን፣ ጥበብንና ከፍታን የሚሞሉበትን፣ፍትህንና ጥንቃቄን የሚያስተምሩበትን ቁርአንን ያነብላቸው ገባ፡፡ እናቱ በአንድ ጥፊ ልታሰቆመው አሰበች፡፡ ግን በሙስዓብ ፊት ላይ ላይጠፋ የበራው የእምነት ብርሃን የተዘረጋችውን ጥፊ ከምንም አልቆጠራትም፡፡ ከእምነቱ ፍንክች እንደማይልና እንደማይመለስ እርግጠኛ ሆኑ፣ ተስፋም ቆረጡ፡፡ ከቤቱ አንዱ ጥግ ላይ አሰረችው፡፡ ተዘጋበት፡፡ እስረኛ ሆነ፡፡ የቅጣትን ዓይነት ከየቀለማቱ አቀመሱት፡፡ እንዳይንቀሳቀስም አገቱት፡፡ በሰንሰለትም ጠፈሩት፡፡ ያላወቁት ነገር ግን ይህ ሁሉ የስቃይ ዶፍ በእምነት በከበረች ነፍስ ፊት ደቃቃና ከንቱ ልፋት መሆኑን ነበር፡፡ ወደ ሐበሻ(አቢሲኒያ) በተደረገው የመጀመሪያው ስደት፣ ከአማኝ ወንድሞቹ ጋር በመሆን ወደ አላህና መልዕክተኛው ሁለተኛው ስደቱን በነጃሺ አፈር ላይ አደረገ፡፡ እዚሁ ሐበሻ ላይ የኑሮ ድርቆሽ ሙስዓብን ክፉኛ አገኘው፡፡ በችግር ሰበብ ወደ መካ ከተመለሱት አንዱም ሆነ፡፡ ከአድቃቂ ድህነት ጋር መኖር ያዘ፡፡ በዐቂዳ ጥላ ስር በውዴታ የሚገኝን ደስታ፣ የመጪውን ዓለም ማብቂያ የለሽ ደስታ እያሰበ፣ የነብዩ ባልደረባ መሆንን እያሰበ ኑሮን ገፋ፡፡ ወራት ያልፋሉ፣አመታት ይነጉዳሉ፡፡ የዚህ ወጣት ችግርና ድህነትም ይጨምራል፡፡ ትእግስትና ፅናትን ጨበጠ፡፡ በአንድ ወቅት ነብዩ(ሰዐወ) ከሌሎች ባልደረቦቻቸው ጋር ተቀምጠዋል፡፡ ሙስዓብ የተቀደደች ብትን ልብስ አጠላልፎ ለብሶ መጣ፡፡ አንዳንድ ቦታ ላይ ሀፍረተ ገላውን ለመሸፈን ሲል በእሾህ ቀጣጥሎታል፡፡ ከብርድና ቅዝቃዜ የተነሳ ሰውነቱ ልክ እባብ ከሞተ በኋላ ክሽ ብሎ እንደሚደርቀው ደርቋል፡፡ የነብዩ(ሰዐወ) ባልደረቦች ሲያዩት በማዘንና መራራት አንገታቸውን ደፉ፡፡ ከእነርሱ ውስጥም እርሱ ያለበትን ችግር ሊቀርፍ የሚችል አቅም ያለው አልነበረም፡፡ ሙስኣብ ሰላምታ አ ቀረበ፡፡ ነብዩም(ሰዐወ) ሰላምታውን ከመለሱ በኋላ እንዲህ አሉ፡- ‹‹ መካ ውስጥ ከቁረይሽ ልጆች ውስጥ ከወላጆቻቸው ዘንድ በፀጋና ምቾት እንዲትረፈረፍ የተደረገ ከሙሰዓብ በቀር አላየሁም፡፡ የአላህና መልእክተኛው ፍቅር ግን ከዛ ውስጥ አወጣው፡፡›› ሙስዓብ ኢብኑ ዑመይር ወደ መዲና የመጀመሪያው የአላህ ነብይ ልኡክ የመጀመሪያው የዐቀባ ቃል ኪዳን ላይ የተሳተፉ ከ12 በላይ የመዲና ሰዎች መካን ለቀው ሲሄዱ ከእነርሱ ጋር ሙስዓብን አብረው ላኩት፡፡ ቁርአንን ያስተምራቸዋል፡፡ የእምነቱን መሰረታዊ ይዘቶች በልቦናቸው ያፀናል በሚል ሀሳብ ማለት ነው፡፡ መዲና እንደደረሱም ሰዒድ ኢብኑ ዙራራ ዘንድ አረፈ፡፡ ወደ አንሷሮች(የመዲና ነዋሪዎች) ዘንድ በመሄድ ወደ አላህና መልዕክተኛው ይጠራቸዋል፡፡ አንድ ሁለት እያለ ብዙ ሰው ወደ ኢስላም ገባ፡፡ አንሷሮች ወደ ኢስላም በገፍ ገቡ፡፡ ሰዒድ ኢብኑ ሙዐዝና ኡሰይድ ኢብኑ ሁዶይር በሙስዓብ እጅ ኢስላምን ተቀበሉ፡፡ ከነርሱ ጀርባ ደግሞ አውስና ኸዝረጅ(መዲና የነበሩ ሁለት ታዋቂ ብሄሮች ናቸው) ሌሎችም ወደ ኢስላም ከተሙ፡፡ ያ ማለት ግን ፈተናዎች አልገጠሙትም ማለት አይደለም፡፡ አንድ ቀን ሰዎችን እያስተማረ ነበር፡፡ ከመዲና ጎሳ አለቆች አንዱ የሆነው ኡሰይድ ኢብኑ ሁዶይር ኢስላምን ሳይቀበል በፊት መጣ፡፡ ኡሰይድ እነዚህን ሰዎች ከዚህ በፊት ስለማያውቁት አንድ አምላክ እየነገረ በእምነታቸው ላይ ጥርጣሬን እያሳደረና እየፈተናቸው ነው በሚል በቁጣ ገንፍሎ እልህ እየገፋው ወደ ሙስዓብ ቀረበ፡፡ ሙስዓብን ከበው ሲማሩ የነበሩ አማኞች መምጣቱን ሲያዩ ርዕደት ያዛቸው፡፡ ፍርሃት ዋጣቸው፡፡ ሙስዓብ ግን የፊቱ ገፅታ እንኳ አልተቀየረም፡፡ አስዓድ ኢብኑ ዙራራ አብሮት ነበር፡፡ ኡሰይድ ተጠጋና ‹‹ ህይወታችሁን ማጣት የማትሹ ከሆነ ደካሞቻችንን ከማጃጃል ታቅባችሁ ከዚህ አካባቢ ጥፉ፡፡ ›› ብሎ በቁጣ ተናገራቸው፡፡ ከሃይሉ ጋር እንደረጋ ባህር፣ እንደንጋት ወጋገን ስንብት በሚመስል መልኩ የሙስዓብ ከናፍሮች ቃላትን አሳምረው ማውጣት ጀመሩ፡፡‹‹ ቅድሚያ ተቀምጠህ ብትሰማንና ጉዳያችንን ከወደድከው ትቀበለዋለህ፣ከጠላኸው ደግሞ እንሄዳለን፡፡›› አለው፡፡ ኡሰይድ የምሉእ አስተሳሰብና አስተውሎት ባለቤት ነበርና ‹‹ልክ ብለሃል›› ብሎ የያዘውን ጦር መሳሪያ መሬት ላይ ጥሎ ተቀመጠ፡፡ ሙስዓብ ቁርአንን ያነባል፡፡ ሙሀመድ ኢብኑ ዓብዲላህ(ሰዐወ) የመጡበትን ጥሪ ይዘት ያብራራል፡፡ የኡሰይድ ግንባር የንጋት ፀሐይ እንዳገኘው መስታወት ያንፀባርቅ ጀመረ፡፡ ከወጣቱ አንደበት የሚወጡት ቃላት ተቆጣጠሩት፡፡ ሙስዓብ ንግገሩን እንደጨረሰ ኡሰይድና አብረው የነበሩት ሰዎች ‹‹ይህ ንግግር ምንኛ ያመረና እውነታ ነው›› አሉ፡፡ ‹‹ወደዚህ እምነት ለመግባ የሚከጅል ሰው ምንድን ነው ማድረግ ያለበት›› አሉም፡፡ ሙስዓብም ‹‹ልብስና አካሉን ያፀዳል፡፡ የአላህን አንድነት ይመሰክራል፡፡›› ሲል መለሰ፡፡ ኡሰይድ ትንሽ ቆይቶ ከፀጉሩ ላይ ውሃ እየተንጠባጠበ መጣና ‹‹ላኢላሃ ኢለሏህ፣ሙሀመደን ረሱሉሏህ›› በማለት መሰከረ፡፡ ዜናው በአንዴ ተዳረሰ፡፡ ሰዒድ ኢብኑ ሙዓዝም መጣ፡፡ ሙስዓብ ዘንድ ጥቂት ተቀመጠ፡፡ ሰምቶት ልቡ ተማረከ፡፡ ኢስላምን ተቀበለ፡፡ ሰዕድ ኢብኑ ዑባዳ ተከተለው፡፡ በነርሱ ኢስላምን መቀበል ፀጋዎች ሞሉ፡፡ የመዲና ነዋሪዎች እርስበርሳቸው ይጠያየቁ ገቡ፡፡ ‹‹ ኡሰይድ ኢብኑ ሁይዶይር፣ሰዕድ ኢብኑ ዑባዳና ሰዕድ ኢብኑ ሙዓዝ ኢስላምን ከተቀበሉ የኛ ወደኋላ ማለት ምንድነው›› አሉ፡፡ ሁሉም ወደ ሙስዓብ ጎረፉ፡፡ ከአንደበታቸው እውነት እንጂ አይወጣም፣እንመን ብለው ኢስላምን ተቀበሉ፡፡ የመጀመሪያው የመልእክተኛው አምባሳደር ተልእኮውን በሚገባ ተወጣ፡፡ ውጤታማም ሆነ፡፡ ሙስዓብ ሰዎችን ጁምዓ ቀን ልሰብስብና ላስተምር፣ላሰግድ የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ ለነብዩ(ሰዐወ) ፃፈ፡፡ ተፈቀደለት፡፡ ሰኢድ ኢብኑ ኸይሰማህ ቤት ሰበሰባቸው፡፡ ይህ እንግዲህ በኢስላም ታሪክ ውስጥ በይፋ ሰውን ሰብስቦ ማስተማር የተጀመረበት አግባብ ነበር፡፡ ሙስዓብ ተልዕኮውን በዚህኛው ሶስተኛው ስደቱ ላይ ሞላ፡፡ ዓመታት ነጎዱ ፣የአውስና ኸዝረጅ ሓጃጆች(የሀጅ ተጓዦች) የሁለተኛውን የዐቀባ ቃልኪዳን ለመፈፀም ወደ መካ መጡ፡፡ ሙስኣብም አብሯቸው መጣ፡፡ የነብዩ(ሰዐወ) ናፍቆት እየገፋው፣ እንባ እያነቀው መካ ገባ፡፡ ወደ ነብዩ (ሰዐወ) ቤት ሮጠ፡፡ አገኛቸው፡፡ የናፍቆት ግንኙነት ነበር…….የአንሷሮችን ሁኔታና እውነታቸውን የሚገልፅ የብስራት ዜና ሪፖርታዥ አቀረበላቸው፡፡ ነብዩም(ሰዐወ) ወደ ካዕባ ተቅጣጭተው ለሁሉም መልካም ነገር እንዲገጥም ዱዓ አደረጉ፡፡ የደስታ ላብም ግንባራቸው ላይ ግጥም አለ፡፡ የሙስኣብ እናት ከመዲና የመምጣቱ ዜና ደረሳት፡፡ ቅድሚያ ታዲያ በጣም ወደናፈቁት ነብይ ቤት እንደሄደም ሰማች፡፡ ‹‹ አንተ ወላጅን አማፂ ቅድሚያ በኔ አትጀምርም እንዴ› › ብላ መልእክት ላከችበት፡፡ ሙስኣብም እንዲህ በማለት በመልእክተኛዋ መልእክትን ላከባት፡፡‹‹ ከአላህ መልዕክተኛ በፊት በማንም አልጀምርም፡፡› የእናት ፍቅሩ ጎተተው፡፡ ሊያያትም ሄደ፡፡ የኑሮ መራር በትር ያረፈበትን ገፅታውን ስታይ አዘነች፡፡ እንዲህም አለች‹‹ ይህ ሁሉ ነገር የደረሰብህኮ ካለህበት ስለሸፈትክ ነው፡፡›› አለችው፡፡ በፍጥነትም ‹‹እኔ ያለሁት በአላህ መልእክተኛ እምነት ኢስላም ላይ ነው፡፡ ይህን እምነት አላህ ለመልእክተናውና አማኞች ወዶታል ፡፡›› ሲል መለሰላት፡፡ ከድንጋጤዋ የተነሳ ክፉ ተናገረችው፡፡ ‹‹እሺ አንዴ ሐበሻ፣ሌላ ጊዜ መዲና እያልክ ምን አመጣህ!›› አለችው፡፡ ራሱን እያወዛወዘ ‹‹በእምነቴ ከምትፈትኑኝ እሸሻችኋለሁ…..››አለ ፡፡ እናቱ ዳግም አግታ የልጇን ወደርሷ መመለስ አሰበች፡፡ ይህንንም ሙስዓብ አወቀባት፡፡ ‹‹እናቴ ልታግቺኝ ብትሞክሪ የሚቀርበኝን ሁሉ ገድላለሁ፡፡›› አላት፡፡ የሙስዓብ ህልፈተ ዜና ቀናት ነጎዱ፣ዓመታት ዙራቸው ከረረ፡፡ ነብዩ(ሠዐወ) ወደ መዲና ተሰደዱ፡፡ ሙስዓብ በንፁህ ልቦናና አንደበት ያመቻቻት የስሪብ(የመዲና ሌላ ስሟ ነው) ተቀበለቻቸው፡፡ መስተንግዶዋንም ጓዳዋን ሁሉ በመስጠት አሳመረች፡፡ የመካ ቁረይሾች ግን ለነብዩ(ሰዐወ) አልተኙም፡፡ መዲና ለምን ትመቻቸው በሚል የጥላቻ ዓይናቸው ቀላ፡፡ ብዙ የግድያ ሙከራ አደረጉ፡፡ የበድር ዘመቻ ተከሰተ፡፡ ብዙ አስተምህሮት ጥሎ በድል አለፈ፡፡ የኡሁድ ዘመቻ መጣ፡፡ ሙስሊሙ ሠራዊት ራሱን ማዘጋጀት ይዟል፡፡ የነብዩ(ሰዐወ) በመሃል ቆመው የእምነት ነፀብራቅ በጥልቅ የሚነበብበትን ፊት እየፈለጉ ነው፡፡ ይህ ፊት እንደተገኘም የኢስላምን ባንዲራ ተሸካሚ አድርገው ሊመርጡት ነው፡፡ ድንገት ሙስዓብን ጠሩት፡፡ መጣ፡፡ ከተከበረው እጃቸው ላይ ትልቅ አደራን ተቀበለ፡፡ አሁን ጦር መስክ ላይ ናቸው፡፡ ፍልሚያው ተጋጋመ፡፡ ተራራን ይጠብቁ ዘንድ የታዘዙት ቀስተኛ ሶሃቦች ትእዛዝ ጣሱ፡፡ አጋሪያን ወደ ኋላ ሲሸሹ ስላዩ ጦርነቱ የተቋጨ መሰላቸው፡፡ ወደ ምርኮ ተጣደፉ፡፡ ጥለውት ከመጡት ተራራ ጀርባ በኩል የኻሊድ ፈረሰኛ ጦር ድንገተኛና ስትራቴጂያዊ ከበባ በማድረግ ሙስሊሙ ሰራዊት ላይ ጥቃት ፈፀመ፡፡ የሙስሊሙን ጦር በተኑት፡፡ ሰልፎቹን በጥሰው ውስጥ ገቡ፡፡ የኢስላምን ቋንጃ ሰብረው መገላገል ቋምጠዋል፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ላይ ተሯሯጡ፡፡ በቀስት ወጓቸው፡፡ ከዙሪያቸው ጥቂት ባልደረቦቻቸቸው ሲከላከሉ ነበር፡፡ ሶሃቦች እዚህም እዚያም ተዋደቁ፡፡ ሙስዓብ የአጋሪያንን ትኩረት ከነብዩ(ሰዐወ) ለመሳብ አደራውን ከፍ አድርጎ አሏሁ አክበር ሲልም ራሱን አንድ አስፈሪ የጦር ብርጌድ አደረገ፡፡ ጥረትና ጭንቀቱ ሁሉ ሙሽሪኮቹን ከነብዩ እይታ ወደርሱ መሳብ ነውና ተሳክቶለት ራሱን ለከፋ አደጋ አጋለጠ፡፡ ህይወት ከነብዩ(ሰዐወ) ውጭ ምን ታደርግና!! አንድ እጁ ባንዲራ ይዞ ታክቢራ ይላል፡፡ ሌላኛው እጁ ደግሞ ሰይፍ ይዞ ይመታል፡፡ ተረባረቡበት፡፡ እስቲ የአይን እማኝ ለነበረው ሹረህቢል አብደሪ እንተወው፡፡ ሙስዓብ የኡሁድ ዘመቻ እለት ባንዲራ ተሸከመ፡፡ ሰራዊቱ ሲርድ እርሱ ግን ፀና፡፡ ኢብኑ ቀሚዓህ የሚባል ፈረሰኛ መጣና ቀኝ እጁን ቆረጠው፡፡ ሙስዓብም ‹‹ሙሃመድ እንዳለፉት መልእክተኞች መልእክተኛ እንጂ ሌላ አይደለም››ይል ነበር፡፡ ባንዲራውን በግራ እጁ ያዘ፡፡ ግራውንም ቆረጠው፡፡ ነገርግን ባንዲራውን በሁለት የተቆረጡ ክንዶቹ መሃል ያዘው(የነቢ አደራ አይደል!)፡፡ ‹‹ሙሃመድ እንዳለፉት መልእክተኞች መልእክተኛ እንጂ ሌላ አይደለም››ማለቱን ቀጥሏል፡፡ በስተመጨረሻም በአንካሴ ወጋው፡ ሙስዓብ ወደቀ፡ ባንድራውንም ለቀቀው፡ የሰማዕታ አንፀባራቂ ፈርጥና ኮከብ ወደቀ፡ አይኔ እያየ ነብዩ(ሰዐወ) ቀድመውኝ ሲሞቱ ማየት አልሻም ይመስል ነበር፡፡ ለርሳቸው የነበረውን ፍቅር ጥልቀት፣የስስቱን መጠን ያሳያል፡፡ አላህም ዝንተዓለም የሚነበብ ቁርአን ይሆን ዘንድ የቁርአን አንቀፅ ይሆን ዘንድ አሟላው፡፡ ‹‹ሙሃመድ እንዳለፉት መልእክተኞች መልእክተኛ እንጂ ሌላ አይደለም…. ›› መራራው ዘመቻ ከተጠናቀቀ በኋላ የቅኑ ሰማዕት አስክሬን ፊት በደም ተለውሶ አፈር ውስጥ ድብቅ ብሎ ተገኘ፡፡ አወዳደቁ ነብዩ(ሰዐወ) የከበቧቸው አጋርያን ገድለዋቸው አስክሬናቸውን ላለማየት ፊቱን በሀዘን ድፍት ያደረገ ይመስል ነበር፡፡ የነብዩን(ሰዐወ) መትረፍ ሳያይ ሰማዕት ሆኖ ወደቀ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ወደ ጦር ሜዳው በመውረድ ሰማዕታትን ተሰናበቱ፡፡ ሙስዓብ ዘንድ ሲደርሱ ግን እምባቸውን መቆጣጠር አቃታቸው፡፡ አለቀሱ…….. ለመስዓብ አስክሬን መከፈኛ ታጣ ኸባብ ኢብኑ አል አረት(ረዐ) እንዲህ ይተርክልናል፡- ‹‹ የአላህን ውዴታ ከጅለን በርሱ መንገድ ወደ መዲና ተሰደድን፡፡ ምንዳችን አላህ ዘንድ ተፅፏል፡፡ ከኛ ውስጥ ምድራዊ ድርሻውን ሳይጠቀም ያለፈ እንደ ሙስዓብ ያለም አለ፡፡ ኡሁድ ቀን ሲገደል መገነዣ ከአንዲት ቁራጭ ፎጣ በቀር ታጣ፡፡ በተገኘቺው ጭንቅላቱን ስንሸፍን እግሩ ይጋለጣል፡፡ እግሩን ስናለብስ ጭንቅላቱ ይታያል፡፡›› ነብዩ(ሰዐወ) ‹‹ከላይ በኩል አልብሱትና ጥሩ ሽታ ባለው ብቃይ እግሩን ሸፍኑት›› አሉ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) የአጎታቸው ሓምዛ መገደልና ሙሽሪኮቹ ገላቸውን መቆራረጣቸው ተደማምሮ ልባቸው በሐዘን ደማ፡፡ ይህ ሁሉ እየሆነ ውስጣቸውን ሐዘን እየበላው የመጀመሪያውን አምባሳደራቸውን አስክሬን ሊሰናበቱት መጡ፡፡ ከአይናቸው እምባ እየረገፈ ‹‹ከአማኞችም ለአላህ ቃል የገቡትን እውን ያደረጉ አሉ፡፡›› ሲሉ ተሰሙ፡፡ የተገነዘባትን ሸካራ ቁራጭ ልብስ እያዩ ‹‹መካ ውስጥ ለስላሳና በጌጥ የተሸቆጠቆጠ ልብስ ለብሰህ አይቼሃለሁ፡፡ ዛሬ ደግሞ ፀጉርህ በአቧራ ተሸፍኖ መገነዣ አጣህ!›› ብለው ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ከፍ ባለ ድምፅ አዋጅ ነገሩ፡፡ ‹‹የአላህ መልዕክተኛ እናንተ ሰማዕታት መሆናችሁን አላህ ፊት የምፅዐት ቀን ይመሰክራሉ፡፡›› አሉ፡፡ ወደተቀሩት ባልደረቦቻቸው ዘወር ብለው‹‹ ሰዎች ሆይ ጎብኟቸው፣ሰላምታም አቅርቡላቸው፡፡ ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታዬ እምላለሁ ማንኛውም ሙስሊም እስከ እለተ ቂያማ ድረስ ሰላምታ አያቀርብላቸውም እነርሱም የሚመልሱ ቢሆን እንጂ፡፡››አሉ፡፡ ሙስዓብ ሆይ! አሰላሙአለይኩም ሰማዕታት ሆይ! አሰላሙ አለይኩም…… የህይወት ታሪኩ ለሰው ልጅ ክብር ነው፡፡ የመስዋዕትነትና ፅኑ እምነት ተምሳሌት ነው፡፡ የሙስዓብ ኢብኑ ዑመይር የኢሥላም ጉዞ ……. ዑመይር በባህረ ሰላጤዋ እምብርት መካ፣ የሁሉ ማረፊያ በሆነው በኢብራሂም የተገነባውን ቤት ካዕባን ከበው ከሚኖሩ ከበርቴዎቿ መሃል አንዱ ነው፡፡ ስልጣንና ሀብት ነበረው፡፡ ታዲያ ደስታና ጫወታ በከበባት በአንዷ ለሊት የመካ ከበርቴዎች ሳቅና ፌሽታ ወደሚንጣት ቤት ተፋጠኑ፡፡ ይህ ሁሉ ታዲያ ዑመይርንና ኸናስ ቢንት ማሊክ የተባለችውን ባለቤቱን እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት ነበር፡፡ አላህ አዲስ ልጅ በመስጠት ከችሮታው ዋለላቸው፡፡ ሙስዐብን መልከ መልካሙን፣ ሙሰዐብን የቁረይሽን ህያው ጌጥን…… ወራት ተፈተለኩ፡፡ዓመታት ነጎዱ፡፡ ታዲያ በእያንዳንዱ የህይወቱ እርከኖች ላይ ምቾትና ተድላ አብረውት ነበሩ፡፡ ከወላጆቹ በኩል የእንክብካቤው ብዛት ምንም እስከማይቀር ድረስ ነበር፡፡ በተለይ እናቱ ከሌሎች ከበርቴ ባልንጀሮቿ ልጆች ጎልቶ እንዲታይ ለውጫዊ ገፅታው ከፍተኛ መዋለ-ንዋይ ታፈስ ነበር፡፡ መካ ላይ የወንድ ውበት ሲነሳ ግንባር ቀደሙ ነበር፡፡ ገፅታው ለእይታ ማራኪና ቆንጆ ነበር፡፡ ሙስዐብ በመካ ጎዳናዎችና መንገድ ጠርዞች ካለፈ እርሱን ለማየት የቆነጃጅትና ውበት አድናቂዎች አንገት ይመዘዛል፡፡ ሙስዓብ ሁሌ ደስተኛና ፈገግታ የማይለየው ለጋ ወጣት ነበር፡፡ ከእድሜው ለጋነትና ውብ ገፅታው የተነሳ የስበሰባዎችና ጥሪዎች ጌጥ ነበር፡፡ ውበቱና የአዕምሮው ብስለት የሸፈቱ ልቦችን የተዘጉ በሮችን ይከፍቱ ነበር፡፡ ወራት ጉዟቸውን ቀጥለዋል አመታትም ቅብብሎሹን አጡፈውታል፡፡ የሙስዓብም የህይወት እሽክርክሪት ቀጥሏል፡፡ ህመም፣ጭንቀትና ችግርን ፍጹም አያውቃቸውም፡፡ ነገር ግን የሙስዐብ እናት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሁሌም የጥልቅ አስተሳሰብን ፋና ታያለች፡፡ከብሩህ ፊቱ ላይ ጥንካሬንና ቆራጥነትን ታነባለች፡፡ ቢሆንም ግን የዚህ ጥንካሬ ምንጩ ርቋታል፡፡ እናት የልጇን ውስጥ የማንበብ ችሎታ ቢኖራትም ይህ ግን ተሳናት፡፡ ቀናት ወደፊት አንድ ሲሉ የሙስዓብም ጥንካሬ ይፈረጥማል፡፡ ዛሬ ያለበት ላይ ሆኖ ያለፉ ቀናቱን ሲያስባቸው አሰልቺ ህልሞችና ቅዠት ሆኑበት፡፡ ከእለታት በአንዱ ቀን ይህ ወጣት ሰዎች ከታማኙ ሙሃመድ ሰምተው የሚያወሩትን ይሰማል፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) አላህ እርሳቸውን አብሳሪና አስጠንቃቂ አድርጎ እንደላካቸው፣ ወደ ብቸኛው ተመላኪ አንድነት ተጣሪ እንደሆኑ ይናገራሉ፡፡ መካ ከተማ ነግቶ በመሸ ቁጥር ጭንቀትና ጉዳይዋ ሙሐመድና ኢስላም ከሆኑ ሰንብቷል፡፡ ታዲያ ይህ በምቾት ክልል ውስጥ ያለው መልካሙ ሙስዓብ የዚህን ወሬ ዱካ ከሌሎች በተለየ መልኩ አፈንፍኖ ነበር የሚሰማው፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ካመኑ ተከታዮቻቸው ጋር በመሆን ከቁረይሽ ረብሻና ማደናቆር ራቅ ብለው ሶፋ ተራራ ስር በሚገኘው አርቀም ቤት ውስጥ እንደሚሠበሠቡ ሠማ፡፡ አላቅማማም፡፡ የማየትና እርጋታ ናፍቆት እየቀደመው ወደ አርቀም ቤት አመራ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ለባልደረቦቻቸው ቁርአንን ያነቡላቸዋል፡፡ ቀጥሎም ለታላቁ አላህ ይሰግዳሉ፡፡ ኢማን በሙስዓብ ልብ ውስጥ ቦታውን ሲይዝ አልቆየም፡፡ ከነብዩ(ሰዐወ) ልቦና ተንቆርቁሮ በከናፍሮቻቸው መሃል የሚወጣው የቁርአን ብርሃናማ መልዕክት ወደሚሰሙ ጆሮዎችና ወደሚያስተነትኑ ህሊናዎች ይፈሳሉ፡፡ በዚህች ምሽት ታዲያ የሙስዓብ ልቦና ተረታ፡፡ አንዳች ነገር ከቆመበት ቦታ ፍንቅል አደረገው፡፡ ያላሰበው የደስታ ስሜት ሊያበረው ቀረበ፡፡ ድንገት ነብዩ(ሰዐወ) ዘንድ ተጠጋ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ)በቀኝ እጃቸው የሙስዓብን ደረት ዳበሱት፡፡ እርግጥ የርሱ እርጋታ ጥልቅ ነበር፡፡ በዓይን እርግብግብታ ቅፅበት የጥበብን ጥግ ከዕድሜው በላይ ተላበሰ፡፡ የዘመናትን የጉዞ መስመር ሊቀይር ታጨ፡፡ እናት ልጇን በሃሳብ ዱካ ትከተለው ጀመር፡፡ ተፈታተነችውም፡፡ ልጅ ግን እርጋታው ይጨምራል፡፡ ዑስማን ኢብኑ ጦልሐ አል ሂንዲ ለእናቱ ኢስላምን እንደተቀበለ ሲነግራት ብዙም አልቆየም፡፡ በእርግጥ ዑስማን ሙስዓብ የነብዩን(ሰዐወ) ዓይነት ስግደት ሲሰግድ አይቶት ነበር፡፡ ሙስዓብ ጥቅልል ብሎ ዳሩል አርቀም(ነብዩ መካ ውስጥ ኢስላምን በድብቅ ያስተማሩበት የመጀመሪያው ቤት ነው)ገባ፡፡ በኢስላማዊ ጥሪ ታሪክና ህይወት ውስጥ ህያው ቅርስ ወደሆነችው ቤት፡፡ በወቅቱ በሙስሊሞች ጉልበት ላይ ተጨማሪ ኃይል ሆነ፡፡የነብዩ(ሰዐወ) ኢስላማዊ ጥሪ ከደሙ ተዋሃደች፡፡ እምነቱን በማንነቱ ላይ ከታች ወደ ላይ ካበው፡፡ ከማመኑ በፊት የነበረበትን ህሊናዊ ጨለማ የኋሊት ቃኘው፡፡ አሁን ስላለበት ኢስላማዊ ብርሃንና ጠንካራ፣ ነፃ ተከታዮቹ አስተነተነ፡፡ የሙስዓብ ኢስላምን መቀበል ትልቅ ስደት ነበር፡፡ ሙስዓብ የመጀመሪያውን ስደት ያደረገው ከምድራዊ ብልጭልጮችና ጌጧ ወደ አላህና መልዕክተኛው ነበር፡፡ የጥልቅ ለውጡ ሚስጥሩም ይኸው ነበር፡፡ መካ ውስጥ የኢስላም ሕንፃ ግንባታ አንድ ጡብ ለመሆን በቃ፡፡ ሙስዓብ ኢስላምን ከመቀበሉ ጋር ተያይዞ ከእናቱ በስተቀር ምድር ላይ የሚፈራው ኃይል አልነበረም፡፡ የእናቱ ነገር ግን አሳሰበው፡፡ አላህ በጉዳዩ ላይ ፍርዱን እስኪያመጣ ድረስ ኢስላምን መቀበሉን መደበቅ እንዳለበት ወሰነ፡፡ ነገር ግን መካ በዚያ ወቅት ምንም ሚስጥር የላትም፡፡ የቁረይሽ ዓይንና ጆሮ በየመንገዱ ላይ መረጃን ይፈልጋል፣ያሰራጫልም፡፡ በእያንዳንዷ የእግር ፋና ላይ ትንታኔ ይሰጣል፡፡ ሙስዓብ እናቱ፣ ቤተሰቦቹና ቅርብ ዘመዶቹ በሙሉ ኢስላምን እንደተቀበለ አወቁበት፡፡ ነገርግን በመኃላቸው ቆሞ በፅናት ነብዩ(ሰዐወ) የተከታዮቻቸውን ልቦና የሚያፀዱበትን፣ ጥበብንና ከፍታን የሚሞሉበትን፣ፍትህንና ጥንቃቄን የሚያስተምሩበትን ቁርአንን ያነብላቸው ገባ፡፡ እናቱ በአንድ ጥፊ ልታሰቆመው አሰበች፡፡ ግን በሙስዓብ ፊት ላይ ላይጠፋ የበራው የእምነት ብርሃን የተዘረጋችውን ጥፊ ከምንም አልቆጠራትም፡፡ ከእምነቱ ፍንክች እንደማይልና እንደማይመለስ እርግጠኛ ሆኑ፣ ተስፋም ቆረጡ፡፡ ከቤቱ አንዱ ጥግ ላይ አሰረችው፡፡ ተዘጋበት፡፡ እስረኛ ሆነ፡፡ የቅጣትን ዓይነት ከየቀለማቱ አቀመሱት፡፡ እንዳይንቀሳቀስም አገቱት፡፡ በሰንሰለትም ጠፈሩት፡፡ ያላወቁት ነገር ግን ይህ ሁሉ የስቃይ ዶፍ በእምነት በከበረች ነፍስ ፊት ደቃቃና ከንቱ ልፋት መሆኑን ነበር፡፡ ወደ ሐበሻ(አቢሲኒያ) በተደረገው የመጀመሪያው ስደት፣ ከአማኝ ወንድሞቹ ጋር በመሆን ወደ አላህና መልዕክተኛው ሁለተኛው ስደቱን በነጃሺ አፈር ላይ አደረገ፡፡ እዚሁ ሐበሻ ላይ የኑሮ ድርቆሽ ሙስዓብን ክፉኛ አገኘው፡፡ በችግር ሰበብ ወደ መካ ከተመለሱት አንዱም ሆነ፡፡ ከአድቃቂ ድህነት ጋር መኖር ያዘ፡፡ በዐቂዳ ጥላ ስር በውዴታ የሚገኝን ደስታ፣ የመጪውን ዓለም ማብቂያ የለሽ ደስታ እያሰበ፣ የነብዩ ባልደረባ መሆንን እያሰበ ኑሮን ገፋ፡፡ ወራት ያልፋሉ፣አመታት ይነጉዳሉ፡፡ የዚህ ወጣት ችግርና ድህነትም ይጨምራል፡፡ ትእግስትና ፅናትን ጨበጠ፡፡ በአንድ ወቅት ነብዩ(ሰዐወ) ከሌሎች ባልደረቦቻቸው ጋር ተቀምጠዋል፡፡ ሙስዓብ የተቀደደች ብትን ልብስ አጠላልፎ ለብሶ መጣ፡፡ አንዳንድ ቦታ ላይ ሀፍረተ ገላውን ለመሸፈን ሲል በእሾህ ቀጣጥሎታል፡፡ ከብርድና ቅዝቃዜ የተነሳ ሰውነቱ ልክ እባብ ከሞተ በኋላ ክሽ ብሎ እንደሚደርቀው ደርቋል፡፡ የነብዩ(ሰዐወ) ባልደረቦች ሲያዩት በማዘንና መራራት አንገታቸውን ደፉ፡፡ ከእነርሱ ውስጥም እርሱ ያለበትን ችግር ሊቀርፍ የሚችል አቅም ያለው አልነበረም፡፡ ሙስኣብ ሰላምታ አ ቀረበ፡፡ ነብዩም(ሰዐወ) ሰላምታውን ከመለሱ በኋላ እንዲህ አሉ፡- ‹‹ መካ ውስጥ ከቁረይሽ ልጆች ውስጥ ከወላጆቻቸው ዘንድ በፀጋና ምቾት እንዲትረፈረፍ የተደረገ ከሙሰዓብ በቀር አላየሁም፡፡ የአላህና መልእክተኛው ፍቅር ግን ከዛ ውስጥ አወጣው፡፡›› ሙስዓብ ኢብኑ ዑመይር ወደ መዲና የመጀመሪያው የአላህ ነብይ ልኡክ የመጀመሪያው የዐቀባ ቃል ኪዳን ላይ የተሳተፉ ከ12 በላይ የመዲና ሰዎች መካን ለቀው ሲሄዱ ከእነርሱ ጋር ሙስዓብን አብረው ላኩት፡፡ ቁርአንን ያስተምራቸዋል፡፡ የእምነቱን መሰረታዊ ይዘቶች በልቦናቸው ያፀናል በሚል ሀሳብ ማለት ነው፡፡ መዲና እንደደረሱም ሰዒድ ኢብኑ ዙራራ ዘንድ አረፈ፡፡ ወደ አንሷሮች(የመዲና ነዋሪዎች) ዘንድ በመሄድ ወደ አላህና መልዕክተኛው ይጠራቸዋል፡፡ አንድ ሁለት እያለ ብዙ ሰው ወደ ኢስላም ገባ፡፡ አንሷሮች ወደ ኢስላም በገፍ ገቡ፡፡ ሰዒድ ኢብኑ ሙዐዝና ኡሰይድ ኢብኑ ሁዶይር በሙስዓብ እጅ ኢስላምን ተቀበሉ፡፡ ከነርሱ ጀርባ ደግሞ አውስና ኸዝረጅ(መዲና የነበሩ ሁለት ታዋቂ ብሄሮች ናቸው) ሌሎችም ወደ ኢስላም ከተሙ፡፡ ያ ማለት ግን ፈተናዎች አልገጠሙትም ማለት አይደለም፡፡ አንድ ቀን ሰዎችን እያስተማረ ነበር፡፡ ከመዲና ጎሳ አለቆች አንዱ የሆነው ኡሰይድ ኢብኑ ሁዶይር ኢስላምን ሳይቀበል በፊት መጣ፡፡ ኡሰይድ እነዚህን ሰዎች ከዚህ በፊት ስለማያውቁት አንድ አምላክ እየነገረ በእምነታቸው ላይ ጥርጣሬን እያሳደረና እየፈተናቸው ነው በሚል በቁጣ ገንፍሎ እልህ እየገፋው ወደ ሙስዓብ ቀረበ፡፡ ሙስዓብን ከበው ሲማሩ የነበሩ አማኞች መምጣቱን ሲያዩ ርዕደት ያዛቸው፡፡ ፍርሃት ዋጣቸው፡፡ ሙስዓብ ግን የፊቱ ገፅታ እንኳ አልተቀየረም፡፡ አስዓድ ኢብኑ ዙራራ አብሮት ነበር፡፡ ኡሰይድ ተጠጋና ‹‹ ህይወታችሁን ማጣት የማትሹ ከሆነ ደካሞቻችንን ከማጃጃል ታቅባችሁ ከዚህ አካባቢ ጥፉ፡፡ ›› ብሎ በቁጣ ተናገራቸው፡፡ ከሃይሉ ጋር እንደረጋ ባህር፣ እንደንጋት ወጋገን ስንብት በሚመስል መልኩ የሙስዓብ ከናፍሮች ቃላትን አሳምረው ማውጣት ጀመሩ፡፡‹‹ ቅድሚያ ተቀምጠህ ብትሰማንና ጉዳያችንን ከወደድከው ትቀበለዋለህ፣ከጠላኸው ደግሞ እንሄዳለን፡፡›› አለው፡፡ ኡሰይድ የምሉእ አስተሳሰብና አስተውሎት ባለቤት ነበርና ‹‹ልክ ብለሃል›› ብሎ የያዘውን ጦር መሳሪያ መሬት ላይ ጥሎ ተቀመጠ፡፡ ሙስዓብ ቁርአንን ያነባል፡፡ ሙሀመድ ኢብኑ ዓብዲላህ(ሰዐወ) የመጡበትን ጥሪ ይዘት ያብራራል፡፡ የኡሰይድ ግንባር የንጋት ፀሐይ እንዳገኘው መስታወት ያንፀባርቅ ጀመረ፡፡ ከወጣቱ አንደበት የሚወጡት ቃላት ተቆጣጠሩት፡፡ ሙስዓብ ንግገሩን እንደጨረሰ ኡሰይድና አብረው የነበሩት ሰዎች ‹‹ይህ ንግግር ምንኛ ያመረና እውነታ ነው›› አሉ፡፡ ‹‹ወደዚህ እምነት ለመግባ የሚከጅል ሰው ምንድን ነው ማድረግ ያለበት›› አሉም፡፡ ሙስዓብም ‹‹ልብስና አካሉን ያፀዳል፡፡ የአላህን አንድነት ይመሰክራል፡፡›› ሲል መለሰ፡፡ ኡሰይድ ትንሽ ቆይቶ ከፀጉሩ ላይ ውሃ እየተንጠባጠበ መጣና ‹‹ላኢላሃ ኢለሏህ፣ሙሀመደን ረሱሉሏህ›› በማለት መሰከረ፡፡ ዜናው በአንዴ ተዳረሰ፡፡ ሰዒድ ኢብኑ ሙዓዝም መጣ፡፡ ሙስዓብ ዘንድ ጥቂት ተቀመጠ፡፡ ሰምቶት ልቡ ተማረከ፡፡ ኢስላምን ተቀበለ፡፡ ሰዕድ ኢብኑ ዑባዳ ተከተለው፡፡ በነርሱ ኢስላምን መቀበል ፀጋዎች ሞሉ፡፡ የመዲና ነዋሪዎች እርስበርሳቸው ይጠያየቁ ገቡ፡፡ ‹‹ ኡሰይድ ኢብኑ ሁይዶይር፣ሰዕድ ኢብኑ ዑባዳና ሰዕድ ኢብኑ ሙዓዝ ኢስላምን ከተቀበሉ የኛ ወደኋላ ማለት ምንድነው›› አሉ፡፡ ሁሉም ወደ ሙስዓብ ጎረፉ፡፡ ከአንደበታቸው እውነት እንጂ አይወጣም፣እንመን ብለው ኢስላምን ተቀበሉ፡፡ የመጀመሪያው የመልእክተኛው አምባሳደር ተልእኮውን በሚገባ ተወጣ፡፡ ውጤታማም ሆነ፡፡ ሙስዓብ ሰዎችን ጁምዓ ቀን ልሰብስብና ላስተምር፣ላሰግድ የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ ለነብዩ(ሰዐወ) ፃፈ፡፡ ተፈቀደለት፡፡ ሰኢድ ኢብኑ ኸይሰማህ ቤት ሰበሰባቸው፡፡ ይህ እንግዲህ በኢስላም ታሪክ ውስጥ በይፋ ሰውን ሰብስቦ ማስተማር የተጀመረበት አግባብ ነበር፡፡ ሙስዓብ ተልዕኮውን በዚህኛው ሶስተኛው ስደቱ ላይ ሞላ፡፡ ዓመታት ነጎዱ ፣የአውስና ኸዝረጅ ሓጃጆች(የሀጅ ተጓዦች) የሁለተኛውን የዐቀባ ቃልኪዳን ለመፈፀም ወደ መካ መጡ፡፡ ሙስኣብም አብሯቸው መጣ፡፡ የነብዩ(ሰዐወ) ናፍቆት እየገፋው፣ እንባ እያነቀው መካ ገባ፡፡ ወደ ነብዩ (ሰዐወ) ቤት ሮጠ፡፡ አገኛቸው፡፡ የናፍቆት ግንኙነት ነበር…….የአንሷሮችን ሁኔታና እውነታቸውን የሚገልፅ የብስራት ዜና ሪፖርታዥ አቀረበላቸው፡፡ ነብዩም(ሰዐወ) ወደ ካዕባ ተቅጣጭተው ለሁሉም መልካም ነገር እንዲገጥም ዱዓ አደረጉ፡፡ የደስታ ላብም ግንባራቸው ላይ ግጥም አለ፡፡ የሙስኣብ እናት ከመዲና የመምጣቱ ዜና ደረሳት፡፡ ቅድሚያ ታዲያ በጣም ወደናፈቁት ነብይ ቤት እንደሄደም ሰማች፡፡ ‹‹ አንተ ወላጅን አማፂ ቅድሚያ በኔ አትጀምርም እንዴ› › ብላ መልእክት ላከችበት፡፡ ሙስኣብም እንዲህ በማለት በመልእክተኛዋ መልእክትን ላከባት፡፡‹‹ ከአላህ መልዕክተኛ በፊት በማንም አልጀምርም፡፡› የእናት ፍቅሩ ጎተተው፡፡ ሊያያትም ሄደ፡፡ የኑሮ መራር በትር ያረፈበትን ገፅታውን ስታይ አዘነች፡፡ እንዲህም አለች‹‹ ይህ ሁሉ ነገር የደረሰብህኮ ካለህበት ስለሸፈትክ ነው፡፡›› አለችው፡፡ በፍጥነትም ‹‹እኔ ያለሁት በአላህ መልእክተኛ እምነት ኢስላም ላይ ነው፡፡ ይህን እምነት አላህ ለመልእክተናውና አማኞች ወዶታል ፡፡›› ሲል መለሰላት፡፡ ከድንጋጤዋ የተነሳ ክፉ ተናገረችው፡፡ ‹‹እሺ አንዴ ሐበሻ፣ሌላ ጊዜ መዲና እያልክ ምን አመጣህ!›› አለችው፡፡ ራሱን እያወዛወዘ ‹‹በእምነቴ ከምትፈትኑኝ እሸሻችኋለሁ…..››አለ ፡፡ እናቱ ዳግም አግታ የልጇን ወደርሷ መመለስ አሰበች፡፡ ይህንንም ሙስዓብ አወቀባት፡፡ ‹‹እናቴ ልታግቺኝ ብትሞክሪ የሚቀርበኝን ሁሉ ገድላለሁ፡፡›› አላት፡፡ የሙስዓብ ህልፈተ ዜና ቀናት ነጎዱ፣ዓመታት ዙራቸው ከረረ፡፡ ነብዩ(ሠዐወ) ወደ መዲና ተሰደዱ፡፡ ሙስዓብ በንፁህ ልቦናና አንደበት ያመቻቻት የስሪብ(የመዲና ሌላ ስሟ ነው) ተቀበለቻቸው፡፡ መስተንግዶዋንም ጓዳዋን ሁሉ በመስጠት አሳመረች፡፡ የመካ ቁረይሾች ግን ለነብዩ(ሰዐወ) አልተኙም፡፡ መዲና ለምን ትመቻቸው በሚል የጥላቻ ዓይናቸው ቀላ፡፡ ብዙ የግድያ ሙከራ አደረጉ፡፡ የበድር ዘመቻ ተከሰተ፡፡ ብዙ አስተምህሮት ጥሎ በድል አለፈ፡፡ የኡሁድ ዘመቻ መጣ፡፡ ሙስሊሙ ሠራዊት ራሱን ማዘጋጀት ይዟል፡፡ የነብዩ(ሰዐወ) በመሃል ቆመው የእምነት ነፀብራቅ በጥልቅ የሚነበብበትን ፊት እየፈለጉ ነው፡፡ ይህ ፊት እንደተገኘም የኢስላምን ባንዲራ ተሸካሚ አድርገው ሊመርጡት ነው፡፡ ድንገት ሙስዓብን ጠሩት፡፡ መጣ፡፡ ከተከበረው እጃቸው ላይ ትልቅ አደራን ተቀበለ፡፡ አሁን ጦር መስክ ላይ ናቸው፡፡ ፍልሚያው ተጋጋመ፡፡ ተራራን ይጠብቁ ዘንድ የታዘዙት ቀስተኛ ሶሃቦች ትእዛዝ ጣሱ፡፡ አጋሪያን ወደ ኋላ ሲሸሹ ስላዩ ጦርነቱ የተቋጨ መሰላቸው፡፡ ወደ ምርኮ ተጣደፉ፡፡ ጥለውት ከመጡት ተራራ ጀርባ በኩል የኻሊድ ፈረሰኛ ጦር ድንገተኛና ስትራቴጂያዊ ከበባ በማድረግ ሙስሊሙ ሰራዊት ላይ ጥቃት ፈፀመ፡፡ የሙስሊሙን ጦር በተኑት፡፡ ሰልፎቹን በጥሰው ውስጥ ገቡ፡፡ የኢስላምን ቋንጃ ሰብረው መገላገል ቋምጠዋል፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ላይ ተሯሯጡ፡፡ በቀስት ወጓቸው፡፡ ከዙሪያቸው ጥቂት ባልደረቦቻቸቸው ሲከላከሉ ነበር፡፡ ሶሃቦች እዚህም እዚያም ተዋደቁ፡፡ ሙስዓብ የአጋሪያንን ትኩረት ከነብዩ(ሰዐወ) ለመሳብ አደራውን ከፍ አድርጎ አሏሁ አክበር ሲልም ራሱን አንድ አስፈሪ የጦር ብርጌድ አደረገ፡፡ ጥረትና ጭንቀቱ ሁሉ ሙሽሪኮቹን ከነብዩ እይታ ወደርሱ መሳብ ነውና ተሳክቶለት ራሱን ለከፋ አደጋ አጋለጠ፡፡ ህይወት ከነብዩ(ሰዐወ) ውጭ ምን ታደርግና!! አንድ እጁ ባንዲራ ይዞ ታክቢራ ይላል፡፡ ሌላኛው እጁ ደግሞ ሰይፍ ይዞ ይመታል፡፡ ተረባረቡበት፡፡ እስቲ የአይን እማኝ ለነበረው ሹረህቢል አብደሪ እንተወው፡፡ ሙስዓብ የኡሁድ ዘመቻ እለት ባንዲራ ተሸከመ፡፡ ሰራዊቱ ሲርድ እርሱ ግን ፀና፡፡ ኢብኑ ቀሚዓህ የሚባል ፈረሰኛ መጣና ቀኝ እጁን ቆረጠው፡፡ ሙስዓብም ‹‹ሙሃመድ እንዳለፉት መልእክተኞች መልእክተኛ እንጂ ሌላ አይደለም››ይል ነበር፡፡ ባንዲራውን በግራ እጁ ያዘ፡፡ ግራውንም ቆረጠው፡፡ ነገርግን ባንዲራውን በሁለት የተቆረጡ ክንዶቹ መሃል ያዘው(የነቢ አደራ አይደል!)፡፡ ‹‹ሙሃመድ እንዳለፉት መልእክተኞች መልእክተኛ እንጂ ሌላ አይደለም››ማለቱን ቀጥሏል፡፡ በስተመጨረሻም በአንካሴ ወጋው፡ ሙስዓብ ወደቀ፡ ባንድራውንም ለቀቀው፡ የሰማዕታ አንፀባራቂ ፈርጥና ኮከብ ወደቀ፡ አይኔ እያየ ነብዩ(ሰዐወ) ቀድመውኝ ሲሞቱ ማየት አልሻም ይመስል ነበር፡፡ ለርሳቸው የነበረውን ፍቅር ጥልቀት፣የስስቱን መጠን ያሳያል፡፡ አላህም ዝንተዓለም የሚነበብ ቁርአን ይሆን ዘንድ የቁርአን አንቀፅ ይሆን ዘንድ አሟላው፡፡ ‹‹ሙሃመድ እንዳለፉት መልእክተኞች መልእክተኛ እንጂ ሌላ አይደለም…. ›› መራራው ዘመቻ ከተጠናቀቀ በኋላ የቅኑ ሰማዕት አስክሬን ፊት በደም ተለውሶ አፈር ውስጥ ድብቅ ብሎ ተገኘ፡፡ አወዳደቁ ነብዩ(ሰዐወ) የከበቧቸው አጋርያን ገድለዋቸው አስክሬናቸውን ላለማየት ፊቱን በሀዘን ድፍት ያደረገ ይመስል ነበር፡፡ የነብዩን(ሰዐወ) መትረፍ ሳያይ ሰማዕት ሆኖ ወደቀ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ወደ ጦር ሜዳው በመውረድ ሰማዕታትን ተሰናበቱ፡፡ ሙስዓብ ዘንድ ሲደርሱ ግን እምባቸውን መቆጣጠር አቃታቸው፡፡ አለቀሱ…….. ለመስዓብ አስክሬን መከፈኛ ታጣ ኸባብ ኢብኑ አል አረት(ረዐ) እንዲህ ይተርክልናል፡- ‹‹ የአላህን ውዴታ ከጅለን በርሱ መንገድ ወደ መዲና ተሰደድን፡፡ ምንዳችን አላህ ዘንድ ተፅፏል፡፡ ከኛ ውስጥ ምድራዊ ድርሻውን ሳይጠቀም ያለፈ እንደ ሙስዓብ ያለም አለ፡፡ ኡሁድ ቀን ሲገደል መገነዣ ከአንዲት ቁራጭ ፎጣ በቀር ታጣ፡፡ በተገኘቺው ጭንቅላቱን ስንሸፍን እግሩ ይጋለጣል፡፡ እግሩን ስናለብስ ጭንቅላቱ ይታያል፡፡›› ነብዩ(ሰዐወ) ‹‹ከላይ በኩል አልብሱትና ጥሩ ሽታ ባለው ብቃይ እግሩን ሸፍኑት›› አሉ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) የአጎታቸው ሓምዛ መገደልና ሙሽሪኮቹ ገላቸውን መቆራረጣቸው ተደማምሮ ልባቸው በሐዘን ደማ፡፡ ይህ ሁሉ እየሆነ ውስጣቸውን ሐዘን እየበላው የመጀመሪያውን አምባሳደራቸውን አስክሬን ሊሰናበቱት መጡ፡፡ ከአይናቸው እምባ እየረገፈ ‹‹ከአማኞችም ለአላህ ቃል የገቡትን እውን ያደረጉ አሉ፡፡›› ሲሉ ተሰሙ፡፡ የተገነዘባትን ሸካራ ቁራጭ ልብስ እያዩ ‹‹መካ ውስጥ ለስላሳና በጌጥ የተሸቆጠቆጠ ልብስ ለብሰህ አይቼሃለሁ፡፡ ዛሬ ደግሞ ፀጉርህ በአቧራ ተሸፍኖ መገነዣ አጣህ!›› ብለው ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡ ነብዩ(ሰዐወ) ከፍ ባለ ድምፅ አዋጅ ነገሩ፡፡ ‹‹የአላህ መልዕክተኛ እናንተ ሰማዕታት መሆናችሁን አላህ ፊት የምፅዐት ቀን ይመሰክራሉ፡፡›› አሉ፡፡ ወደተቀሩት ባልደረቦቻቸው ዘወር ብለው‹‹ ሰዎች ሆይ ጎብኟቸው፣ሰላምታም አቅርቡላቸው፡፡ ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታዬ እምላለሁ ማንኛውም ሙስሊም እስከ እለተ ቂያማ ድረስ ሰላምታ አያቀርብላቸውም እነርሱም የሚመልሱ ቢሆን እንጂ፡፡››አሉ፡፡ ሙስዓብ ሆይ! አሰላሙአለይኩም ሰማዕታት ሆይ! አሰላሙ አለይኩም……
9004
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A4%E1%89%BD%E1%8A%A0%E1%8B%AD%E1%89%AA
ኤችአይቪ
ኤችአይቪ ቫይረስ የሰውነትን የበሽታ መከላከያ በተለይ የነጭ ደም ሴሎችን (ህዋሳትን) በማጥቃት በቀላሉ ሰውነት ለበሽታ እንዲጋለጥ የሚያደርግ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ ያለባቸው ሰዎች የበሽታው ምልክት ሳይታይባቸው ለብዙ ዓመታት መኖር ይችላሉ። ቫይረሱ በሰውነታ ውስጥ እስከ አስር ዓመት በመቆየት ምንም ሳይታውቅ እና ምንም አይነት የህመም ምልክት ሳይታይበት በመኖር እና አለማውቅ ከአንድ ሰው ወደሌላ ሰው ሊተላለፍ የሚችል አደገኛ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ የሚያጠቃው ኤችአይቪ የሚያጠቃው የሰውነት የነጭ የደም ሴሎችን የሰውነት የበሽታ የመከላከያ ተቁዋማትን ነው። የሲዲፎር በመባል የሚታውቀውን የሰውነት የነጭ የደም ሴል ቁጥሩን () ከ 200 በታች በማድረግ የቫይረሱ መጠን በደም ውስጥ እንዲጨምር በማድረግ ለሕይወት ኣደገኛ እና ምቹ ጊዜ ተባቂ በመባል የሚታውቁትን በሸታዎች (ኦፓርቹንስቲክ ኢንፈክሽስ . በመፍጠር ኤድስ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ያደርጋል። ኤድስ ማለትም ኣኳየርድ ኢምዩኖደፊሸንሲ ሲንድረም ሲሆን ኤድስ ኤችእይቪ የማያማጣው የመጨረሻ ደረጃ ነው። ኤችአይቪ ያለበት ሰው ኤድስ ደረጃ ላይ ለመድረስ ብዙ ዓመታት ይወስድበታል። እንዲሁም መድኃኒቱንም ሳይጅምር ኤድስ ደረጃ ሳይደርስ ብዙ ዓመታት ሊቆይ ይችላል። አንድ ሰው የኤድስ ደረጃ ላይ ደረሰ ማለት የኤችአይቪ ቫይርስ የበሽታ መከላከያ ሃይል ተቁዋማትን ደምስሶ እና ሰውነታችን ከማንኛውም በሽታ የመቋቋም ኃይሉን በማሳጣት ለተለያዩ ኢንፈክሽኖች ይጋለጣል። አንድ ሰው አንድ ወይም ሁለት ኢንፌክሽኖች ሲኖሩበት እና በጣም ዝቅያለ የቲ-ሴል ቁጥር ሲኖረው ያሰው የኤድስ ደረጃ ደረሰ ሊያስብለው ይችላል። የኤችአይቪ አመጣጥ ሳይንቲስቶች የኤችአይቪን ቫይረስ አመጣጥ እንደጠቆሙት ከሆነ ከዌስት አፍሪካ ከሚገኝው ቺፓንዝ ዝርያ የመጣ መሆኑን አሳወቀዋል። ይህውም ሊሆን የቻለው የሰው ልጅ ቺፓንዚን ለምግብነት በሚይድንበት ጊዜ በሚደረገው የደም ንክኪ መሰርት ቫይርሱ ሊተላለፈ እንደቻለና። ከብዙ አመት በሃላም ቀስ በቀስ ወደ መላው አለም ሊስፋፋ እንደቻለ ገልጽዋል ኤችአይቪ ቀስ በቀስ እየተስፋፋ የመጣው ከ1978 (፲፱፻፸ ዓ.ም.) ወዲህ ነው። በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ውስጥ 1.3 ሚሊዮን በላይ የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤችአይቪ ቫይርስ ጋር አብረው ይኖራሉ። በዓለም ላይም ከ 25 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች በኤድስ በሚመጣ በሸታ ተይዘው ሞተዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዬጵያ ውስጥ የኤድስ ታማሚዎች መኖራችው የተረጋገጠው በ1978 ዓ/ም ነው። በ2006ዓ/ም ወደ 2.9 ሚሊዮን የሚጠጉ ወንዶች፤ ሴቶች እና ሕጻናትም ሕይወታቸውን አተዋል። ኤችአይቪ ከተያዙት ውስጥ ከግማሸ በላይ የሚገምቱት ሲሞቱ 39.5 ሚሊዮን የሚሆኑ ከቫይርሱ ጋር በመኖር ይገኛሉ። በቅርቡ በ እንደተዘገበው 4.3 ሚሊዮን የሚጠጉ አዲስ ሰዎች በኤችአይቪ እንደተያዙ ይገልጻል። ኤችአይቪ መተላለፊያ መንገዶች የኤች አይቪ ቫይረስ ከሰውንት ከውጣ በሃላ በጣም ደካማ ከመሆኑ የተነሳ ብዙ አይቆይም ወድያውኑ ይሞታል። በዛ የተነሳ ነው ኤችአይቪ ከማንም ሰው ጋር በምናደርጋቸው የዕለት ተለት እንቅስቃሴዎች ለምሳሌ፣ እንደ እጅ መጨባበጥ፣ መተቃቅፍ፣ እና መሳሳም ሊያስተላልፉ እንደማይችሉና። በተጨማሪም ኤች አይቪ በመጸዳጃ ቤት መቀመጫ፣ በበር መኽፈቻ፣ በብርጭቆ መጠጫ፣ በምግብ ወይም በማንኛውም አይነት እንስሳ እንደ ቢንቢ ንክሻ በመሳሰሉት ሊይዝ አይችልም። ኤችአይቪ ለመያዝም ሆነ ለማስተላለፍ የሚችሉበት መንገዶች የተለያዩ ናቸው፣ መንገዶቹ ምን እንደሆኑ ማወቁ በጣም ጠቀሜታ አለው። ስለ ኤችአይቪ ዕውቀት ያለውን ሰው ማነጋገር ተገቢ ሆኖ ሳለ ይህንንም ከታች የተዘርዘረውን በተግባር ላይ ቢያውሉት መልካም ነው፣ ኤችአይቪ በሚከተሉት ሁኔታዎች ሊተላለፍ ይችላል ቫይረሱ ያለበት ሰው የተጠቀመበትን የድረግ () መርፌ ሌላ ሰው ቢጠቀምበት () ቫይረሱ ሊተላለፍ ይችል። ቫይረሱ ካለበት ማንኛውም ሰው (ወንድ ወይም ሴት) ጋር የግብረ ሰዶም ግንኙነት () በማድረግ በሽታው ሊይዝ ይችላል። ቫይረሱ ካለበት ሰው ጋር በሚደረግ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ( ኤችአይቪ ያለባት እናት ቫይረሱን (ማህፀን ውስጥና በወሊድ ጊዜም) ለሕፃንዋ ማስተላለፍ () ትችላለች። ቫይረሱ የለባት እመጫትን ጡት ወተት ካጠባች ቫይረሱን ሊተላለፍ ይችላል። መከላከያ እርምጃዎች 4ቱ " መ" ዎችይ ለመከላከል የሚከተሉትን እርምጃዎች መውሰድ በጣም ጠቃሚ ነው ከኤችአይቪ ቫይረስ ለመከላከል የሚከተሉትን እርምጃዎች መውሰድ ይጠቅማል ከማንኛውም ዓይነት የግብረ ሥጋ ግንኙነት (ከተቻለ) መቆጠብ፣ ካልተቻለ ኣንድ ታማኝ የፍቅር ጓደኛ ጋር በመወሰን ኮንዶም መጠቀም ለረዥም ጊዜ ተማምነው ኣብረው የቆዩ ባልና ሚስት በመስጋትና ለኤችአይቪ ይይዘኛል በሚል ፍራቻ በኮንዶም () መጠቀም የለባቸውም። ታማኝነት ከመቼውም ጊዜ በላይ ኣስፈላጊ ስለሆነ ባለትዳሮች ታማኝንታችውን ማጎልበት ይጠበቅባቸዋል የሚወጉ ድራጎች (እየተደበቁ ተሰባስበው ባልፀዱ መሣሪያዎች ከሚወስዱ ጋር) አለመውሰድ ማለት መርፌና ሲሪንጋ ኣለመጋራት ከማያውቁት ሰው ወይም ከብዙ ሰዎች ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ካደረጉ ከሌላ ሰው ጋር ምንም አይንት ግንኙንት ከመፈጽም በፊት መመርመራ ያድርጉ ለገንዘብ ብለው ከማያቁት ሰው ጋር ማንኛውንም ዓይነት የግብረ ሥጋ ግንኙነት ኣለማድረግ ኤችአይቪ ለመያዝ የሚያስችሉ ባህሪዎች ዋነኞቹ -በጣም አስጊ ደረጃ ላይ ሊሆኑ የሚችሉ የሚወጉ ድራጎች (እየተደበቁ ተሰባስበው ባልፀዱ መሣሪያዎች ከሚወስዱ ብዙ ሰዎች ጋር) መርፌና ሲሪንጋ ከተጋሩ ልቅ የሆነ የግብረ ሥጋ ግንኙነት፣ የግብረ ሰዶም ግንኙነት () ከፈጸሙ ለገንዘብ ብለው የግብር ሥጋ ግንኙንት ወይም የግብረ ሰዶም ግንኙነት ከፈጸሙ ለአባላዘር በሽታ ተጋለጠው የሚያቁ ከሆነና ወይም ከላይ የተዘርዘሩትን ከፈጸመ ግለሰብ ጋር የወሲባዊ ግኑኘንት ከፈጸሙ የኤችአይቪ ምርመራ እርግጠኛ ዕራስን ለማወቅ ግዴታ መልሱ የሚገኘው የኤችአይቪ ምርመራ በማድረግ ብቻ ነው። ስለዚህ ዕራሶን የሚጠራጠሩ ከሆነ ተመርመሩ። ተመርምረው ውጤቶን ከቫይረሱ ነፃ መሆኖ ቢነገሮትም የውሽት ውጤት የሚባል (ዊንዶ ፔሬድ የሚባል) ነገር ስላለ ከ 3-6 ወር በሃላ እርግጠኛ ለመሆን ደግመው መመርመር ይገባል። ይህን ሲያረጉ ግን አሁንም ኮንዶም መጠቀሞን ኤችአይቪ ቀስ በቀስ እየተስፋፋ የመጣው ከ1978 (፲፱፻፸ ዓ.ም.) ወዲህ ሲሆን እስከ 1985 ድረስ የተበከለ ደም ናሙና በመወጋትና በመሳሰሉት ብዙ ሰዎች ይዚህ ሰለባ በመሆን ብዙ ሰዎች ተይዘዋል። ከ1988 ወዲህ ግን ኤችአይቪ ሲኖር ደም ውስጥ ነጭ ሴል የሚሠራውን ኣንቲቦዲ () በመመርመር ኤችአይቪ ቫይረስ እንዳለ እና እንደሌለ የሚጣራበት ፈጣን የምርመራ ዘዴ ስለተሠራ በሆስፒታል ከሚሰጠን ደም መተላለፉ ቀርትዋል። ከአካል የሚወጡ ፈሳሾች ላይ ሁሉ ኤችአይቪን ማግኝት የሚቻል ቢሆንም መደበኛ የኤችአይቪ ምርመራ በደም ናሙና ላይ የሚደረግ የኤችአይቪ-1/2 አንቲ ባዲ ምርመራ ነው። እስታሁን የተሰሩትን የአንቲባዲ ምርመራ አይነቶችን በሁለት ከፍል ማየት ይቻላል። ኤላይዛ መሰረት አርገው የሚከናወኑ ኤላይዛ አይ.ኤፍ.ኤ ኤላይዛ-ዌስተርን ቦሎት ፈጣን ምርመራዎች የሚባሉት ተመርተው በገበያላይ የቀርቡ ወደ 60 የሚቆጠሩ መመርመሪያዎች ሲኖሩ በሶስት ዋና ዋና ቴክኒኮች ላይ የተመረኮዙ ናችው። ፓርዲክል አጉሌሽን ( ላተራል ፍሎ ( ፍሎ ትሩ ( እነዚህ መመርመሪያዎች እያንዳንዳቸው ለምርመራ ማከናወኛነት በምንጠቀምበት ጊዜ ምንም አይነት ተጨማሪ ኪሚካል አያስፈልጋቸውም። ለመጠቀምም ጊዜ የማይፈጅና ዋጋውም ተመጣጣኝ ነው። አስተማማጝነታቸውም ከኤላይዛር ጋር የሚስተካከል ነው። ፈጣን የኤችአይቪ ምርመራ ማለት ለቫይረሱ የተዘጋጀ አንቲ ቦዲ በደም ውስጥ መኖሩንና አለመኖሩን የሚያመልክት የምርመራ አይነት ነው። በፈጣን የምርመራ ዘዴ ውጤቱን ከ10-60 ደቂቃዎች ውስጥ ማውቅ የሚያስችል የመመርመሪያ ዘዴ ነው። ተመርምረው ውጤቶዎ ኤችአይቪ ፖዘቲቨ ከሆነስ በአሁኑ ጊዘ በኤችአይቪ ዙሪያ ላይ በዙ መረጃዎች የሚገኘበት ግዘ ስለሆነ ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር ተስማምቶ ለመኖርይቻላል። በአሁን ሰአት ኤችአይቪን እንደማንኛውም አይንት ቫይረስ አይቶ ጤናን እየጠበኩና መንፈስን ሳያስጨንቁ ተረጋግቶ መኖር ይቻላሉ። ኤችአይቪ እንዳይዘን የምንከላከልበት ክትባት በአሁኑ ሰአት የለም። ኤችአይቪ ከያዘም በኋላ የሚፈውስ መድኃኒት የለም። ነገር ግን ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር ተስማምቶ ለመኖር የቻላለ። በአሁኑ ጊዜ ፀረ-ኤችአይቪ መዳኒቶች ከፈተኛውን አስታውጾ በማድረግ ላይ የገኛሉ። ኤችአይቪ ያለበት ሰው በትክክል የፀረ-የኤችአይቪ መዳኒቶቹን በመውሰድ እንደማንኛውም ሰው መኖር ይችላል። ቫይርሱ ያለባቸው ሰዎች መውለድ ሲፈልጉ ተገቢውን የህክምና አገልግሎት ከጤና ባለሙያቸው ጋር በመነጋገር ጤነኛ ልጀ መውለስ ይችላሉ። ኤችአይቪ ያለባት እናትከማርገዝዋ በፊት ማወቅ የሚገባትን ቅድመ ተከተሎች መከተል ይኖርባታል። ኤችአይቪ እንዴት እንደሚተላለፍ መረጃዎችን በመከታተል ቫይረሱ እንዳይሰራጭ ትክክለኛዎቹን ጥንቃቄዎች መከተልና ለሌሎችም ማስተማር የያንዳንዳችን ኃላፊነት መሆን አለበት። ኤችአይቪ እንዴት እንደሚተላለፈ ግንዛቤዎች እንዴት እንደምንከላከል መረዳትና ወደ ሌሎች እንዳይተላለፍ እንዴት መጠንቀቅ እንዳለብን ማወቅ በጣም ጠቃሚ ነው። እንዳይስፋፋ መከላከል መታቀብ (ከማንኛውም አይነት የገብረስጋ ግንኙነት መቆጠብ) እንድ የትዳር ጛደኛ እስከሚያገኙ ድረስ ወይም ደሞ ኤችአይቪ እንዳለባችሁ ካወቃችሁ ሁለት ኤችአይቪ እንዳለባቸው ያወቁ ባለትዳሮች ወይም አበረው ያሉ ጉዋድኞች በግብረ-ሥጋ ግንኙነት ጊዜ ኮንዶም መጠቀም አለባቸው ምክንያቱም ከተለያዩ የአባላዘር በሽታዎች ለመከላከል እና ከተለያዩ የኤችአይቪ ንዑስ ዝርያዎች ላለመያዝ ከሁለት አንዳቸው ብቻ ከሆኑ ኤችአይቪ ያለበት ሁልጊዜ ኮንዶም መጠቀም እና ቅባት () ያለው ኮንዶም መጠቀም ወይ ደሞ ከአንድ ሰው በላይ ጋር የግብረ-ሥጋ ግንኙንት የሚፈጸሙ ከነበሩ ወይም ከሆኑ፦ የኤችአይቪ ምርመራ ያድርጉ ወንድ ከሆኑ እና ከወንድ ጋር የግብረ-ሰዶም ግንኙነት ፈጸመው ከሆነ ቢያንስ ቢያንስ በአመት አንዴ ይመርመሩ ሴት ከሆኑ እና ለማርገዝ እቅድ ካሎት ወይም ካርገዙ በአስቸኩዋይ ይመርምሩ (ጤነኛ ልጅ ለመውለድ ሲባል) የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ከመፈጸሞ በፊት ስለ ኤችአይቪ እና ሰለ ተለያዩ የአባላዘር በሽታዎች ከወንድ/ከሴት ጛድኛ ጋር በግልጽ ማውራት ልምድ ማረግ አለብን በደንብ ተጠናኑ፣ ተወያዩ ስለ ሁለታችሁም ስለ አለፈው የወሲብ ሕይውታችሁ ውይም ድራግ ትጠቀሙ ከነበረ ( መጠጥ፣ ጫት ሱሰኝነት) ሌሎችም ከዚህ በፊት የኤችአይቪ ምርመራ አርገው እንደሚያቁና እንደማያቁ መጠያየቅ ምንም እንኩዋን የኤችአይቪ እያዛለሁ ብለው ምንም ጥርጣሬ ባይኖሮትም ሁሌ ለጠቅላላ ምርመራ በሚሄዱበት ጊዜ የኤችአይቪ ምርመራ ቢያረጉ በጣም ጠቃሚ ነው የውጭ መያያዣዎች አበሻ ኬር የበጎ እድራጊ ድርጅት 20, 2008 ትርጉም በአበሻ ኬር ? ትርጉም በአበሻ ኬር የኢትዮጲያ ኤድስ መረጃ ማእከል ኣበራ ሞላ ዶ/ር ኣበራ ሞላ
41766
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%8D%88%E1%88%AB%20%E1%8B%88%E1%88%8D%E1%8B%B0%E1%88%B0%E1%88%9B%E1%8B%95%E1%89%B5
ተፈራ ወልደሰማዕት
የክቡር አቶ ተፈራ ወልደሰማዕት የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣን ነበሩ። ከ1976 ዓ/ም አንስተው እስከ 1982 ድረስ በኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስትር ሥልጣንና በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ በከፍተኛው የአመራር ቦታ ላይ ነበሩ። የህይወት ታሪካቸው ክቡር አቶ ተፈራ ወልደሰማዕት ከአባታቸው ከአቶ ወልደሰማዕት ማረሚ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ጀማነሽ በዳኔ በሰሜን ሸዋ ቅምቢብት ወረዳ እ. ኤ. አ. መስከረም 1 ቀን 1938 ዓ.ም ተወለዱ። አቶ ወልደሰማዕት እና ወይዘሮ ጀማነሽ ሶስት ወንድ ልጆችን ተገኝ፥ በቀለ ፥እና ተፈራን እና ሁለት ሴቶችን ጥሩነሽ ፥ እና ዘነበችን ያፈሩ ሲሆን ተፈራ የመጨረሻ ልጅ ናቸው። ክቡር አቶ ተፈራ የተወለዱበት ወቅት ግፈኛው ፋሺሽት ኢጣልያ ኢትዮጵያን የወረረበት እና ሕዝብዋን በመርዝ ጋዝ የፈጀበት ስለነበረ አቶ ወልደሰማዕት ዘምተው በጦር ሜዳ ግዳጃቸውን ከተወጡ በኋላ ወደ መኖሪያ አካባቢያቸው ተመልሰው ብዙም ሳይቆዩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። እንዳካባቢው ህዝብ ሁሉ ወ/ሮ ጃማነሽም ልጆቻቸውን ይዘው ከመኖሪያ ስፍራቸው ተሰደዋል። ክቡር አቶ ተፈራም አዲስ አበባ ተወስደው የአገራቸውን የቤተክህነት ትምህርት በመከታተል ዳዊት እስከመድገም ድረስ ደርሰዋል። ከዚያም ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ካክብ ፅባህ ትምህርት ቤት ገብተው ከአንደኛ አስከ አስራ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርትን አጠናቀዋል። ቀጥለውም ለአንድ ዓመት በመምህርነት ከአገለገሉ በኋላ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ገብተው በኢኮኖሚክስ የባችለር ዲግሪ በማዕረግ () በማግኘት እ.ኤ.አ. በ1964 ዓ.ም. ተመርቀዋል። ከኮሌጅ እንደተመረቁም በሕዝባዊ ኑሮ ዕድገት ሚኒስቴር ተቀጥረዋል። በዚህም መስሪያ ቤት ለተወሰነ ጊዜ ከሰሩ በኋላ ወደ ሔግ ኔዘርላንድ ለከፍተኛ ትምህርት ተልከው እ. ኤ. አ. በ 1967 ዓ.ም. በልማት ኢኮኖሚክስ የማስተርስ ዲግሪ አግኝተዋል። ከዚያም ወደ ሕዝባዊ ኑሮ ዕድገት ተመልሰው የፕላን ዩኒቲን በማቋቋምና የዩኒቲ ሃላፊ በመሆን የረጅም ጊዜ የልማት ፕላን እና ዓመታዊ የካፒታል ፕሮግራም እና በጀት በማዘጋጀት እ. ኤ. አ ከ1967 እስከ 1971 አገልግለዋል፡፡ ከዚያም ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር በማዛወር በዋሺንግተን በኢትዮጵያ ኤምባሲ የኢኮኖሚ እና ፋይናንስ አማካሪ ሆነው እ. ኤ. አ. 1972-1974 ዓ.ም. ሰርተዋል በዚህም ሓላፊነታቸውን ከአለም ባንክ ከአይ. ኤም. ኤፍ ከአሜሪካ የኢንተርናሽናል የልማት ድርጅት ማለትም ከዩ. ኤስ. ኤይድ እና ከሌሎችም ድርጅቶች ጋር ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን ዕርዳታ እያደገ አንዲሄድ ክትትል አድርገዋል። ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ተመልሰው እ. ኤ. አ. ከ 1974-1975 ዓ.ም. በገንዘብ ሚኒስቴር የብድር አና ኢንቨስትመንት መምርያ ሃላፊ በመሆን የውጪ ብድር አና እርዳታን አንዲሁም በተለያዩ የፐብሊክ ኢንተርፕራይዞች የመንግስት ኢንቨስትመንተ ይዞታ ተከታትለዋል። ቀጥሎም እ. ኤ. አ ለ 1977-1982 በዚሁ መ/ቤት በምክትልነትና በተጠባባቂነት ከዚያም እ. ኤ. አ. ከ 1977-1982 ዓ.ም. በገንዘብ ሚንስቴር ከፍተኛ አገልግሎት አበርክተዋል። በዚህም ሓላፊነታቸው የሚኒስቴርነት ከፍተኛ አገልግሎት አበርክተዋል። በዚህም ሐላፊነታቸው የሚነስቴሩን ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች በአዲስ መልክ በማደራጀት ለአገሪቷ የልማትና ቋሚ ወጪዎች የሚውሉ ገቢዎችን በማሳደግ እና ሌሎች ሚኒስቴሮችም የቀለጠፈ የበጀት አሰጣጥ አገልግሎት እንዲያገኙ አንዲሁም በፋይናንስ ቁጥጥር እና በጥናት እና ምርምር ሚኒስቴሩ እንዲጠናከር እና የሚጠበቅበትን ወቅታዊ እና የተሟላ አገልግሎት እንዲያበረክት ከማንኛውም ጊዜ ይበልጥ ከኢንተርናሽናል እና ከአህጉራዊ ድርጅቶች በተለይም ከዓለም ባንክ አና ከአፍሪካ ልማት ባንክ ከተለያዩ አገሮች ለኢትዮጵያ ልማት ዕርዳታ እና ብድር ለማስገኘት ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። እንደሚታወቀው ጊዜው አጅግ ፈታኝ የለውጥ እና የሽግግር ወቅት ስለነበር የአገሪትዋ የፋይናንስ ሁኔታ እንዳይናጋ በብልህነት በጥንቁቅነት በማስተዳደር የበጀት ዲሲፕሊን እንደተጠበቀ እንዲቆይ በለውጡም ምክንያት ለኢትዮጵያ ከምዕራብ አገሮች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሚሰጠው የወጪ ዕርዳታ እንዳይቀንስ ከፍተኛ ተጋኢደሎ አድርገዋል። በወቅቱ አዲስ የኢትዮጵያ ወዳጅ ከሆኑት አንፃር ለፖለቲካ ተቀጋይነት ሳይሆን የአገሪቱን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚያስችል የኢኮኖሚ ግንኙነት እንዲጠበቅ ተዋግተዋል። በዚህም የተነሳ በአፍሪካም ሆነ በኢንተርናሽናል ደረጃ ብዙ አድናቆት እና አክብሮት አትርፈዋል። አብሮዋቸው የነበሩ የስራ ጓደኞቻቸውም ለዚሁ ሁሉ ምስክር ናቸው። ክቡር አቶ ተፈራ የገንዘብ ሚኒስትር በነበሩበት አመታት ሁሉ የብሔራው ባንክ የቦርድ ሊቀመንበር ስለነበሩ የአገሪቷን አጠቃላይ የሞንተሪ እና የፋይናንስ የበላይ ሓላፊ በመሆን የሚጠበቅባቸውን አመራር በብቃት ሰጥተዋል። ከላይ ከተዘረዘሩት ቋሚ የስራ ሓላፊነታቸው በተጨማሪ የብሔራዊ ፕላን ኮሚሽን ፥የካቢኔው የኢኮኖሚ አና ሕግ ኮሚቴዎች የቴሌኮሚኒኬሽን፥ የብሔራዊ ቡና ፥የከብት እርባታ እና የስጋ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦርዶች አባልም ሆነው አገልግለዋል። ክቡር አቶ ተፈራ በትዕግስት፥ በብልህነት እና በቅንነት እጅግ ከባድ የሆነውን ሓላፊነታቸውን በመወጣት ለብዙ ዓመታት ከአገለገሉ በኋላ የአገሪቷ ሁኔታ ከመሻሻል ይልቅ ወደባሰ አቅጣጫ እያመራ መሄዱን በመገንዘባቸው እ.ኤ.አ 1982 ዓ.ም. ቤተሰባቸውን ይዘው ወደ አሜሪካ በመምጣት ከስራቸው በገዛ ፈቃዳቸው ተሰናብተዋል። በረጅም ጊዜ የአገልግሎት ዘመን የቀሰሙትን ሰፊ የስራ ልምድ በተለይ በፋይናንስ አና ባንክኒግ በበጀት በጥናት እና ምርምር ከፍተኛ ፖሊስ ነክ የምክር አገልግሎት ለ 10 ዓመታት ያህል ለልዩ ልዩ አገሮች እና ድርጅቶች አበርክተዋል። ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል። በዋሽንግተን ለሚገኘው ኦቨር. ሲይስ. ዲቨሎፕመንት ካወንስል () እ.ኤ.አ. ከ1982-1983 ዓ.ም. በመመደብ ከሰሓራ በታች ያሉት የአፍሪካ አገሮች () የልማት ዕድገት በሚመለከት ጥናት አካሂደዋል። በአይ. ኤም. ኤፍ ተመድበው ለስወዚላንድ መንግስት ብሄራዊ ባንክ እ.ኤ.አ. ከ 1984-1987 ዓ.ም. የጥናት እና ምርምር አቅሙ የጥናት እና ምርምር አቅሙ ስለሚዳብርበት በማማከር ሰርተዋል። በዓለም ባንከ አማካሪ በመሆን ስለአፍሪካ ፐብሊክ ኢንተርፕራይዞች የስራ ክንውን እና የማሻሻያ ጥናት እ. ኤ. አ. በ1988 አካሂደዋል። በአይ. ኤም. ኤፍ ተመድበው ለሌሴቶ ማዕከላዊ ባንክ በፖሊሲ እና ኦፕሬሽን በጥናት እና ምርምር የባንኩ አቅም ስለሚጠናከርበት አማክረዋል። አይ. ኤም. ኤፍ እና የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት ለናሚቢያ መንግስተ የሚሰጡትን የቴክኒክ ዕርዳታ በማስተባበር እና ለናሚቢያ የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ በመሆን አገልግለዋል። ክቡር አቶ ተፈራ ከአበረከትዋቸው ጽሁፎች መካከል በልማት ኋላቀር ከሆኑ አገሮች መካከል ስለጋምቢያ ሌሴቶ ማላዊ እና ሱዳን ኢኮኖሚ ጥናት (እ. ኤ. አ. 1981) ከሰሓራ በታች ስላሉት አፍሪካ አገሮች የልማት ፖሊሲ ( እ. ኤ. አ 1983) በኢትዮጵያ ልምድ ላይ የተመሰረተ ስለ አንዳንደ የአፍሪካ አገሮች አጀስትመንት () ፖሲሲ ከሌሎች ጋር በመተባበር የአፍሪካ ፐብሊክ ኢንተርፕራይዞች ስለሚሻሻሉበት ጥናት (እ. ኤ. አ. 1989) ስለ ሳዴግ አባል አገሮች የሞኒተር ውህደት/ ህብረት ስለ ናሚቢያ ፊዚካል ፖሊሲ (እ. ኤ. አ 1995)። ይህ ጥናት በናሚቢያ ካቢኔ ጸድቆ ተግባር ላይ ውሏል። ክቡር አቶ ተፈራ ከአፍሪካ አገልግሎታቸውን አጠናቀው ዋሺንግተን ወደ አይ.ኤም. ኤፍ ዋና መስሪያ ቤት በመመለስ በልዩ ልዩ ክፍላተ በመጨረሻም በጡረታ እስከተገለሉ ድረስ የፕላን እና የበጀተ ከፍተኛ በላሙያ በመሆን ሰርተዋል። ክቡር አቶ ተፈራ የ42 ዓመት የትዳር ጓደኛቸው ከሆኑት ከውድ ባላቤታቸው ከወ/ሮ ንግስተ ጌታቸው ሁለት ወንዶቸን ዶ/ር ሄኖክ ተፈራ፥ አቶ ዮሴፍ ተፈራንና እና አንድ ሴት ወይዘሪት ነፃነት ተፈራን አፍርተዋል። ሶስት የልጅ ልጆችንም ለማየት ታድለዋል። ክቡር አቶ ተፈራ ወልደሰማዕት በተመደቡባቸው የስራ ኃላፊነቶች ሁሉ ቅንነት ታማኝነት ጥንቁቅነት እና ለአገር እና ለወገን ተቆርቋሪነትን የሚያንጸባርቅ ጠባይ ነበራቸው። አቶ ተፈራ በዚህች ዓለም አኗኗራቸው እና አረማመዳቸው ሁሉ ኃላፊነት የሚሰማቸው እና ለቤተሰባቸው ፍጹም ፍቅርና እንክብካቤ የሚያደርጉ ለወዳጆቻቸውም በሚፈለጉበት ጊዜ ፈጥኖ ደራሽ ነበሩ። ህልፈት ህይወት ክቡር አቶ ተፈራ ወደሚወድዋት አገራቸው ኢትዮጵያ ዘመዶቻቸውን እና ወዳጆቻቸውን ለማየት ሄደው ባለፈው መጋቢት ወር ወደ ዋሺንግተን እንደተመሉ የጤና መታወክ ገጥሟቸው በምርመራ ላይ እንዳሉ በድንገት እ. ኤ. አ. 25 ቀን 2013 ከእኩለ ሌሊት በኋላ በተወለዱ በሰባ አራት ዓመታቸው በቦልቲሞር ከተማ ባለው በጆነስ ሆፕኪንስ ሆስፒታል ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ሕመም ላይ በቆዩበት ጊዜ የውድ ባላቤታቸው እና የልጆቻቸው እንክብካቤ አንድም ቀን አልተለያቸውም፡፡ ዋቢ ምንጮች የኢትዮጵያ ካቢኔ አባላት
38657
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%89%BB%E1%8A%A8%E1%88%8D
ማቻከል
ማቻከል በአማራ ክልል የሚገኝ ወረዳ ነው። የማቻከል ወረዳ የማቻከል ወረዳ በአማራ ክልል ምስራቅ ጐጃም ዞን ውስጥ ከሚገኙ 18 ወረዳዎች መካከል አንዱ ሲሆን በሰሜን ስናን ወረዳ በደቡብ ደ/ኤልያስ፣ በምዕራብ ደንበጫ ወረዳና በምስራቅ የጐዛምን ወረዳ ያዋስኗቷል፡፡ የወረዳው ርዕሰ ከተማ የሆነችው አማኑኤል ከአዲስ አበባ በተዘረጋው የአስፖልት መንገድ ላይ የምትገኝ ሲሆን ከሃገሪቱ ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ 328 ኪ.ሜ ፣ በክልሉ ርዕሰ ከተማ ባህርዳር 234 ኪ.ሜ እንዲሁም የዞኑ ከተማ የሆነችው ደብረ ማርቆስ 30 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ በወረዳው 24 ቀበሌዎች፣ 3 ንዑስ ከተማና በ1 የከተማ ቀበሌ የተከፋፈለ ሲሆን የወረዳው ዋና ከተማ አማኑኤልም በ1886 በደጃዝማች ጓሉ እንደተቆረቆረች ይነገራል፡፡ የማቻከል ወረዳ አጠቃላይ የቆዳ ስፋት 73558 ሄ/ር ሲሆን የአየር ፀባይ ሁኔታ 58.76 % ደጋ ፣39.1% ወይናደጋ 2.12% ውርጭና 0.02% ቆላ እንዲሁም ከባህር ወለል በላይ 1200-3200 ሜትር ከፍታ አለው፡፡ አማካኝ የሙቀት መጠኑ ከ22 የሚደርስ ሲሆን ከ1500-1800 ሚሊ ሜትር አመታዊ የዝናብ መጠን ይኖረዋል፡፡ በወረዳው ወ 6488 ሴት 66017 በድምሩ 130998 ህዝብ የሚኖር ሲሆን ከነዚህም መካከል ወንድ 59266 ሴት 60406 በድምሩ 119669 የሚሆነው ህዝብ በገጠር የሚኖር ነው፡፡ ሁሉም የወረዳው ህዝብ መቶ በመቶ የአማረኛ ቋንቋ ተናጋሪ ሲሆን 98.98 የኦርቶዶክስ ክርስትና 1.02 የሚሆነው ደግሞ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ነው፡፡ የወረድዋ ህዝብ በአብዛኛው ኑሮው የተመሰረተው በግብርናው ክፍለ ኢኮኖው በተለይም በእርሻ ስራ ላይ ሲሆን ጥቂቶች ደግሞ በንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ፡፡ ከወረዳው ጠቅላላ ስፋት ውስጥ 46372.19 ሄ/ር መሬት ለእርሻ ሰብል፣ 7648 ሄ/ር መሬት ለግጦሽ ፣ 4654 ሄ/ር መሬት በደን የተሸፈኑ ሲሆን ቀሪው ደግሞ በልዩ ልዩ ቆጥቋጦዎች፣ አትክልትና ወንዞች የተሸፈነ ነው፡፡ የአፈር አይነቱም 12.7% መሬት ጥቁር አፈር፣ 5.7% ግራጫ፣ 70.2% ቀይ አፈርና 11.35% ቡናማ አፈርን ያካተተ ነው፡፡ ይህም በወረዳው ውስጥ ለሚመረቱ የአገዳ ፣የብዕርና የቅባት ሰብሎች ምቹ ስብጥር እንዳለው ያመላክታል፡፡ በወረዳው ውስጥ 51 ቅድመ መደበኛ ፣ 72 የጐልማሶች ትምህርት ቤት ፣ 51 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፣ 2 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ፣1 የመሰናዶ ት/ቤት ፣ 1 የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ይገኛሉ፡፡ በጤናው ዘርፍም 6 ጤና ጣቢያዎች እና በሁሉም ቀበሌዎች የጤና ኬላዎች ያሉ ሲሆን አንድም እናት በወሊድ ምክንያት አትሞትም የሚለውን መርህ ከግብ ለማድረስም 1 የቀይ መስቀልና 1 የጤና በድምሩ 2 አንቡላንሶች ለወረዳው ህዝብ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ አጠቃላይ ሃገራዊና ወረዳዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን የተሳለጡ ለማድረግ እንደ ማንኛውም አካባቢ ህ/ሰቡ ግብር የመክፈል ልምዱ እየዳበረ የመጣ ሲሆን በገጠር 23715 ግብር ከፋይ አርሶ አደርና በከተማ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋይ 13 ፤ የደረጃ “ለ” 168 ፤ ደረጃ “ሐ” 1149 በድምሩ 1330 የሚሆኑ ነጋዴ ግብር ከፋዮች ሲኖሩ በተያዘው የበጀት አመትም ከ12 ሚሊዩን 56 ሸህ 40 ብር ግብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁን 7 ሚሊዩን 759 ሽህ 627 ብር ከ18 ሳንቲም ለመሰብሰብ ተችሏል፡፡ ይህም የእቅዱን 64.36 በመቶ ማለት ነው፡፡ከመጠረተ ልማት ዝርጋታ አንፃር ስንመለከት የወረዳውን ከተማ ጨምሮ ቀበሌዎች የ24 ሰዓት የመብራት ተጠቃሚ ናቸው፡፡ በወረዳው ውስጥ በሁሉም ቀበሌዎች የኔትወርክ ዝርጋታ በመኖሩ የተንቀሳቃሽ ስልክ ተጠሟ መሆን ችሏል፡፡ ዋና ከተማውን ጨምሮ በድምሩ 8 ቀበሌዎች የ24 ሰዓት የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ ናቸው ካሉ ቀበሌዎች ከ18 በላይ የሚሆኑት በጋ ከክረምት አገልግሎት በሚሰጡ መንገዶች ከወረዳ ማቻከል ጋር የተገናኙ ናቸው፡፡ በወረዳው ውስጥ የተለያዩ ታሪካዊና ባህላዊ ቦታዎች የሚገኙ ሲሆን1880 ዓ.ም በንጉስ ተክለሃይማኖት ዘመን ቆሎቤና ሰሎሜ በተባሉ ጣልያዊያን እንደተሰሩ የሚነገርላትና 6 ሜትር ከፍታ 4 ሜትር ስፋትና 4 ሜትር ርዝመት ያለው የአድያ ድልድይ በዘመኑ በነበሩ ሰዎች በአበያ በረሃ ድንጋይ በማምጣት የተሰሩ በመሆኑ ቀልብን ይስባል፡፡ የኳሽባ ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም ከተፈጥሯዊ መስህብነት ባለፈ በአትክልትና ፍራፍሬ ተሸፍኖ በልማት ስራውም ሊጐበኝ የሚገባ ሌላው የቱሪስት መስህብ ሲሆን የጨኔ አንድነት ብሮግን እቅዱስ ላሊበላ አንድነት ገዳም ሌላው ተፈጥሯዊና ማራኪ ገዳም የወረዳው እንቁና ማራኪ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የማቻከል ወረዳ ለነዋሪዎቹ ምቹ፣ ለጐብኝዎቹ እንግዳ ተቀባይና ማልማት ለሚፈልጉ የአየር ፀባዩ ተስማሚ የሆነ ተፈጥሯዊ ስነ ምህዳር በጋን ሰርቶ ለመለወጥ ተነሳስቶ ያለው ሰው አክባሪ ህዝብ ያለበት በመሆኑ ወደ ወረዳችን ደግመው ደጋግመው ይመጡና ያልመጡ ይጐብኙ ይዝናኑ፡፡ ህዝብ ቆጠራ አማራ ክልል የኢትዮጵያ ወረዳዎች
32835
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%AD%E1%88%96%E1%8B%8B
ይሖዋ
ይሖዋ በዕብራይስጥ ቋንቋ በመባል በአራት ፊደላት (ሲነበቡ ዮድ ሔ ዋው ሔ) የተጠቀሰው የፈጣሪ ስም በአማርኛ የተለመደ አጠራር ነው። የጥንት አይሁዳውያን በነበራቸው ወግ መሰረት ይህንን ስም በአደባባይ መጥራት እንደ ትልቅ ኃጢአት ስለሚቆጠር ከዚህ ወግ በፊት የነበሩት አይሁዳውያን (በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጽፈው የምናገኛቸው ግለሰቦችም ጭምር) ይህን ስም እንዴት አድርገው የጠሩት እንደነበር ማወቅ አልተቻለም። በ1879 የታተመው የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ በዘጸዓት 6፡3 ላይ "እግዚአ-ይሆዋ" () በማለት ይህንን ስም አስቀምጧል። አብዛኞቹ ዘመናዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች በአንዳንድ ቦታዎቻቸው ላይ "ያህዌ" ወይም "ያህዌህ" የሚለውን አጠራር የተጠቀሙ ሲሆን በአጠቃላይ "እግዚአብሔር" በሚለው ቃል መጠቀምን መርጠዋል። መለኮታዊው ስም - አስፈላጊነቱና ትርጉሙ በመጽሐፍ ቅዱስህ ውስጥ መዝሙር 83፡18 የተተረጎመው እንዴት ነው? ታዋቂው የኪንግ ጀምስ እንግሊዝኛ ትርጉም ይህን ጥቅስ "ሰዎች ሁሉ ስምህ ይሖዋ () የሆነው አንተ፣ በምድር ሁሉ ላይ አንተ ብቻ ልዑል እንደሆንህ ይወቁ።" ሲል ተርጉሞታል። በርከት ያሉ ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞችም ተመሳሳይ በሆነ መንገድ ተርጉመውታል። ይሁን እንጂ ብዙዎቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ይሖዋ የሚለውን ስም "እግዚአብሔር"፣ "ጌታ" ወይም "ዘላለማዊ" እንደሚሉት ባሉ የማዕረግ ስሞች ተክተውታል። ይህ ጥቅስ የሚናገረው ስለ ስም ነው። አብዛኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በተጻፈበት በዕብራይስጥ ቋንቋ እዚህ ጥቅስ ላይ በአይነቱ ልዩ የሆነ የግል ስም ሠፍሮ ይገኛል። ይህ ስም በዕብራይስጥ ፊደላት (የሐወሐ) ተብሎ ተጽፏል። በአማርኛ የተለመደው የዚህ ስም አጠራር "ይሖዋ" ነው። ይህ ስም የሚገኘው በአንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ላይ ብቻ ነውን? አይደለም። መጀመሪያ በተጻፉት የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ 7000 ጊዜ ያህል ተጠቅሶ ይገኛል! የአምላክ ስም ምን ያህል አስፈላጊ ነው? ኢየሱስ ክርስቶስ ያቀረበውን የናሙና ጸሎት እንመልከት። ጸሎቱ የሚጀምረው "በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፤ ስምህ የቀደስ" በሚሉት ቃላት ነው።(ማቴዎስ 6፡9) ከጊዜ በኋላም ኢየሱስ "አባት ሆይ፣ ስምህን አክብረው" ሲል ወደ ፈጣሪ ጸልዮአል። "አክብሬዋለሁ፤ ደግሞም አከብረዋለሁ" የሚል መልስም ከሰማይ መጥቷል። (ዮሐንስ 12፡28) የአምላክ ስም ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነገር እንደሆነ በግልጽ መረዳት ይቻላል። ታዲያ አንዳንድ ተርጓሚዎች ይህን ስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞቻቸው ውስጥ በማውጣት በማዕረግ ስሞች የተኩት ለምንድነው? ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ያሉ ይመስላል። አንደኛው ምክንያት ብዙዎች 'ስሙ መጀመሪያ ይጠራበት የነበረው መንገድ ዛሬ ስለማይታወቅ ልንጠቀምበት አይገባም' የሚል አቋም ያላቸው መሆኑ ነው። የጥንቱ የዕብራይስጥ ቋንቋ የሚጻፈው ያለ አናባቢ ነበር፣ (ልክ የጥንቱ የግእዝ ቋንቋ አጻጻፍ ያለ አናባቢ ይጻፍ እንደነበረው)። ስለሆነም ዛሬ የሐወሐ የሚሉት ፊደላት በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን እንዴት ይነበቡ እንደነበር በእርግተኝነት የሚያውቅ የለም። ይሁን እንጂ ይህ የአምላክን ስም እንዳንጠቀም ሊያግደን ይገባልን? በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን ኢየሱስ የሚለው ስም ይጠራ የነበረው የሹዋ ወይም የሆሹዋ ተብሎ ሊሆን ይችላል፤ በአሁኑ ጊዜ ይህን በእርግጠኝነት ሊናገር የሚችል ሰው የለም። ሆኖም ዛሬ በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ ሰዎች በቋንቋቸው የተለመደውን አጠራር በመጠቀም ኢየሱስ የሚለውን ስም በተለያየ መንገድ ይጠሩታል። ለምሳሌ ጂሰስ በእንግሊዝኛ፣ የሱስ ወይም ኢየሱስ በአማርኛ፣ ያሱ ወይም ያሹ በብዙ የአፍሪካ ቋንቋዎች፣ የሆሹዋ በዕብራይስጥ፣ ኢሳ በአረብኛ፣ የሱሳ በተለያዩ የኢትዮጵያ ደቡብ አካባቢ ቋንቋዎች የኢየሱስ ስም በተለያየ መንገድ ይጠራል። ሰዎች በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበረውን አጠራር ስለማያውቁ ብቻ በዚህ ስም ከመጠቀም ወደኋላ አላሉም። በተመሳሳይም ወደ ውጭ አገር ብትሄድ የራስህ ስም በሌላ ቋንቋ ለየት ባለ መንገድ እንደሚጠራ ትረዳ ይሆናል። ስለዚህም ብዙ ሰዎች የአምላክ ስም ጥንት ይጠራበት የነበረውን መንገድ በእርግጠኝነት አለማወቃችን በስሙ እንዳንጠቀም ምክንያት ሊሆነን አይችልም የሚል አመለካከት አላቸው። የአምላክ ስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲወጣ ምክንያት እንደሆነ ተደርጎ የሚጠቀሰው ሁለተኛው ነገር ለረጅም ዘመን ከኖረ የአይሁዳውያን ወግ ጋር የተያያዘ ነው። ብዙዎች አይሁዳውያን የአምላክ ስም ፈጽሞ መጠራት የለበትም የሚል እምነት አላቸው። ይህ እምነት የሚከተለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ በተሳሳተ መንገድ ከመተርጎም የመነጨ እንደሆነ ካለው ሁኔታ መረዳት ይቻላል፦ "የእግዚአብሔር (የይሖዋ) አምላክህን ስም ያለአግባብ አታንሳ (ወይም በከንቱ አትጥራ)፤ እግዚአብሔር (ይሖዋ) ስሙን ያለ አግባብ የሚያነሳውን በደል አልባ አያደርገውምና።" - ዘጸዓት 20፡7 ይህ ህግ የአምላክን ስም ያለ አግባብ (በከንቱ) መጠቀምን ወይም መጥራትን ያወግዛል። ይሁን እንጂ ስሙን አክብሮት በተሞላበት መንገድ እንዳንጠቀም በፍጹም አይከለክልም። የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሁፎችን (ብሉይ ኪዳንን) የጻፉት ጸሐፊዎች በሙሉ አምላክ ለጥንት እስራኤላውያን በሰጠው ሕግ ይመሩ የነበሩ ታማኝ ሰዎች ናቸው። ሆኖም የአምላክን ስም በተደጋጋሚ ጊዜያት ይጠቀሙ ነበር። ለምሳሌ ያህል በብዙ አምላኪዎች ፊት በታላቅ ድምጽ ይዘመሩ በነበሩ ብዙ መዝሙራት ውስጥ የአምላክን ስም ጠቅሰዋል። እንዲያውም ይሖዋ አምላክ አምላኪዎቹ ስሙን እንዲጠሩ ያዘዛቸው ሲሆን ታማኝ አገልጋዮቹም ይህንን ትዕዛዝ አክብረዋል። (ኢዩዔል 2፡32፣ የሐዋርያት ስራ2፡21) ስለዚህ ዛሬ ያሉ ክርስቲያኖች ኢየሱስ እንዳደረገው የአምላክን ስም አክብሮት በተሞላበት መንገድ መጠቀም ይችላሉ። መጽሐፍ ቅዱስ
16106
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%9E%E1%88%AB%E1%88%B5%E1%89%B0%E1%88%AD%20%E1%8D%8D%E1%8A%AB%E1%88%AC%20%E1%8A%AD%E1%8D%8D%E1%88%8D%20%E1%8D%AB
የዞራስተር ፍካሬ ክፍል ፫
ክፍል ፫ "ከትልቁ ተራራየ ፊት ቆምኩ፣ ከሩቁም መዋተቴ እንዲሁ። ለዛም ስል መጀመሪያ ወደ ጥልቁ ገደሌ፣ ወደ የሚያመኝ ስፍራ፣ ወደጥቁሩ ጎርፌ መውርድ አለብኝ" በማለት ዞራስተር ከተከታዮቹ ተለይቶ ከባዱን ስራውን ለመፈጸም ባዘነ። ግቡም የ"በላይ ሰው"ን ማስተማር አቁሞ እራሱ የበላይ ሰው ለመሆን ነበር። "መሰላል ከሌላችሁ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መወጣጣትን ልመዱ፤ በሌላስ በምን መንገድ ወደላይ ለመውጣት ትሻላችሁ? በጭንቅላታችሁ፣ ከልባችሁ እርቃችሁ... ከዋክብቶቻችሁ ሳይቀሩ ከግራችሁ በታች እስኪሆኑ ወደ ላይ ተወጣጡ!" ዞራስተር በከተሞችና በባህር ጠረፎች በሚዋትትበት ዘመን መንፈሱን ወደታች ስለሚጎትተው የስበት ሃይል ማውጣት ማውረድ ጀመረ። ይህ ሃሳቡን ወደታች የሚጎትተው መንፈስ ባለፈው ክፍል አዋቂው የነገርው የ«ሁሉ ነገር ከንቱነት ነበር። ሁሉም ወደ ላይ የተወረወረ ነገር ወደ መሬት መልሶ ይወድቃል፣ ስለሆነም ሁሉም የከንቱ ከንቱ ነው!» ዞራስተር ይህን ወደታች የሚጎትት የስበት ሃይል ለማሸነፍ የሁሉ ነገር ዘላለማዊ መመላለስን ሃሳብ ማውጣት ማውረድ ጀመረ። በአለም ላይ ያለው የቁስ ብዛት የተወሰነ ሲሆን ጊዜ ግን የማያልቅ ጅረት ነው። ስለሆነም በቁስ ውስጥ ያሉት እያንዳንዱ አተሞች የሚደረደሩበት መንገድ ስፍር ቁጥር ባይኖርውም... ከጊዜ ወሰን የለሽ የትየለሌንት አንጻር እያንዳንዱ የአቶም አደራደር ዘዴ ተመልሶ ይመጣል። እያንዳንዱ ቁስ ያለፈበትን አደራደር በዘመናት ይደግማል። ሁሉም ነገር ተመልሶ ይመጣል። ሁሉም ኅልው ነገር ካሁን በፊት ኅልው ነበር ስለዚህ መጭው ዘመን እንደ በፊቱ ነው። "ኦ! ዞራስተር" አሉ እንስሳቶቹ "ሁሉም ነገር ይሄዳል፣ ሁሉም ነገር ተመልሶ ይመጣል፣ ለዘላለም የህልውና ጎማ ይሽከረከራል። ሁሉም ይሞታል፣ ሁሉም እንደገና ያብባል፣ የህይወት ቀለበት በንዲህ መልኩ ለዘላለም ይቀጥላል። ሁሉም ይሰበራል፣ ሁሉም እንደገና ይጋጠማል፣ ላለም እስከ ዘላለም አንድ አይነት የኅልውና ቤት ይገነባል። ሁሉም ይለያያል፣ ሁሉም ከሁሉ ጋር እንደገና ይገናኛል፣ ለዘለዓለም የኅልውና ቀለበት በራሱ ላይ እንዲህ ይሽከረከራል።" ጊዜ እንደ መስመር ቀጥ ብሎ የተሰመረ ሳይሆን፣ ላለም እስከ ዘላለም ክብ ሰርቶ በራሱ ላይ የሚሽከረከር እንጂ። "ቀጥ ያለ ሁሉ ውሸት ነው፣ ሁሉም እውነት የተንጋደደ ነው! ጊዜ ራሱ ክብ ነው!" ነገር ግን የዘላለም መመላስ ዞራስተርን ከማስደስተ ይልቅ በጣም በጠበጠው። በዚህ ፍልስፍና መሰረት ሁሉ የሰው ልጅ የበላይ-ሰው ለመሆን የሚያደርገው ጥረት መና ሆነ እንደገና ወደ ነበረበት ዝቅተኛ ስብእና ጊዜውን ጠብቆ ይመለሳል። የበላይ ሰው ማለት የሰው ልጅ በትግል የወጣው ተራራና ከዚህም ተራራ ተነስቶ ወደ የበለጠ ከፍታ የሚወጣጣበት ሳይሆን በአዙሪት ውስጥ ያለ አንድ አልባሌ ነጥብ ሆነ። ሃሳቡ ዞራስትራን ክፉኛ አውኮት ሲቆዝም የአንድ ወጣት እረኛ ታሪክ በራዕይ መልኩ ታየው። እረኛው ጉሮሮ ውስጥ ጥቁር እባብ ተሰንቅሮ መተንፈሻ አሳጣው። እባቡንም ከጉሮሮው መንግሎ ለማውጣት የማይቻል ሆነ። በዚህ ጊዜ ዞራስተር ድምጹን ከፍ አድርጎ "እራሱን ግመጠው!" ብሎ ለዕረኛው ጮኽ። ዕረኛውም የተባለውን በማድረግ የእባቡን እራስ ቱፍ ሲል የነጻነትን ሳቅ ያቀልጠው ጀመር። ከዚህ ጀምሮ ዞራስተር አንድና አንድ አላማ ብቻ ህይወቱን ገዛ፣ እርሱም ወደታች የሚጎትተውን መንፈስ በማሸነፍ ልክ እንደ እረኛው የነጻነቱን ሳቅ መሳቅ። ዞራስተር ከብዙ ጉዞ በኋላ ከተራራው ዋሻ ደረስ። በዚህ ክፍል መጨረሻ ዞራስተር ያወከውን ወደታች የሚጎትተውን መንፈስ ሲያሸንፍ እናነባለን። የዘላለም መመላስን ተስፋ አስቆራጭ ሃሳብ ያሸነፈው እንዲህ ነበር፡ ጊዜ ክብ ከሆነ፣ እክቡ የትኛው ላይ ኅልው እንደሆን (የት ላይ እንደምንኖር) ምንም ለውጥ አያመጣም፣ በየትኛው የዕድገት ደረጃ ላይ ኅልው መሆናችንም ምንም ለውጥ አያመጣም፣ "ሁሉም ቅጽበት ላይ ኅልውና ይጀመራል... መካከሉ ሁሉም ቦታ ነው።" ብዙ ሰወች ባለፈው ዘመን ይኖራሉ (ማለት በትውፊት፣ ባህል፣ ካለፉት ዘመናት በተወረሱ የግብረገብ ህግጋት፣ ወዘተ...ስር)። ዞራስተር ደግሞ ወደፊት በሚመጣው፣ ባልተፈጠረው አለም ባህል ይኖር ነበር። ሆኖም ግን ዞራስተር እንደተገነዘበ ያለፈውና መጭው ዘመን ምንም ዋጋ የላቸውም፣ ህይወትን መኖር በአሁኗ ቅጽበት ነው። የህይወት ትግል የሚካሄደው በዚች ቅጽበት ሲሆን ህይወትም የሚገለጸው ኗሪው በትግሉ ውስጥ በሚያሳየው ብርታት ነው። ከዚህ አንጻር የዘላለም ምልልስ ተስፋ የሚያስቆርጥ ጽንሰ ሃሳብ ሳይሆን ከሃይማኖት ውጭ የሆነ አዲስ አይነት የሚያሰደስት ዘላለማዊነት ሆነ። ስለሆነም ዞራስተር ከነበረበት ተውከት ዳነ። ለዚህም ሲል መዝፈንና መደነስ ጀመረ። መዝፈንና መደነስ ከመናገር አንጻር የበለጠ ሃይል አላቸው፡ መናገር ከሰውነታችን የተቆረጠ፣ የንቃተ ኅሊና ስራ ሲሆን መዝፈንና መደንስ ግን ከሰውነታችን ጋር የተያያዙ እንቅስቃሴወች ስለሆኑ ንቃተ-ኅሊናንና አካላታችንን አንድ ላይ የሚያሳትፉ ስራወች ናቸው። መዝፈንና መደነስ የሚችል ሰው ሙሉ ስለሆነ ህይወቱም ከአዋቂ አስተማሪወች ይልቅ በአሁኗ ቅጽበት የሚካሄድ ነው። ዞራስተር አስተማሪ በነበረበት ጊዜ የተሰማው ጎደሎነት ከዚህ አንጻር ነው። መዝፈንና መደነስ ባለመቻሉ ጎድሎ ነበር። ለማጠቃለል ያክል፣ የመጽሃፉ የመጀመሪያ ክፍል የ"በላይ ሰውን" መምጣት የሚሰብክ ሲሆን፣ እጅግ በለመለሙና ጣፋጭ በሆኑ እይታወች የታጀበ ነበር። ክፍሉ ከተዘበራረቀው የባህል ፍርክስካሽ የተስተካከለ ስልጣኔን ለመገንባት የሚጥር ነው። ሆኖም ሁሉም የተስተካከለ ነገር የተሸሸገ ዝብርቅርቅ አስከፊ ነገር ስላለው፣ ይህም አስከፊ ነገር ዞሮ ዞሮ እራሱን የበላይ ስለሚያደርግ፣ ይህን መጋፈጥ ግድ ይላል። የአፖሎ ቀን ያለ ዳዮኒስ ጭለማ ኅልው አይሆንም። ማታው እንዳውም ከቀኑ በጣም ሃይለኛ ነው። እኒህ ጭለማ የሆኑ የህይወት ኃይሎች እጅግ ሃይለኛ ስለሆኑ ሰወች ብዙ ጊዜ ከህይወት መራቅ ይመርጣሉ፣ ስለዚህም በብዙወች አስተያየት ህይወት እጅግ ስቃይ የበዛበትና መጥፎ ሲሆን፣ ኑሮ መሸነፍ ያለበት ነገር ነው ብለው ያምናሉ። የዞራስተር አላማ እንግዲህ ምንም እንኳ ህይወት ብዙ ጊዜ ሽብር ቢኖረውም፣ መጥፎውም ቢበዛም ህይወት መኖር ያለበትና መደገፍ ያለበት እንደሆነ ማሳየት ነው። የመጽሃፉ የመጨረሻ ክፍል የዋናወቹ ገጸ ባህርያት ወደ ህይወትን ከነሽብሩና ጭለማው መውደድን ሽግግር ይተርካል። ከብዙ ማሰብና ማስተማር በኋላ - ህይወትን መኖር፣ ህይወትን ማፍቀር። የሚያይ፣ የሚሰማው፣ የሚያውቅ ፍቅር። ከዘላለም መመላለስ በተጨማሪ ኒሼ ስለ አዳዲስ ህግጋት/ዋጋወች ማውጣት በዚሁ ክፍል አጥብቆ አስተምሯል። "በተሰባበሩና ግማሽ ድረስ በተጻፈባቸው ጽላቶች ተከብቤ ተቀምጨ እጠባበቃለሁ። ከቶ መቼ ይሆን የኔስ ጊዜ?" መደብ :የዞራስተር ፍካሬ
41469
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%A3%E1%88%AB
ሣል
ለፊልሙ፣ ሳራን ይዩ። ሣራ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት የአብርሃም ሚስትና የይስሐቅ እናት ነበረች። በዑር ከላውዴዎን ተወልዳ ስሟ በመጀመርያ ሦራ (ወይም በዕብራይስጡ ሣራይ፥ «ልዕልቴ») ሲሆን በኋላ እግዚአብሔር ወደ «ሣራ» (ዕብራይስጥ ሣራህ፥ «ልዕልት») ቀየረው። በኦሪት ዘፍጥረት 20፡12 ዘንድ፥ አብርሃም ለጌራራ (ፍልስጥኤም) ንጉሥ ለአቢሜሌክ እንዳለው፣ ሣራ የአባቱ (ታራ) ልጅ ሆና በእውነት እህቱ ነበረች። በኩፋሌ 10፡47 ደግሞ አብራም የአባቱን ልጅ ሦራን እንዳገባት ይገልጻል። (ይህ አይነት ትዳር በእግዚአብሔር ሕገጋት የተከለከለው በሕገ ሙሴ ገና ወደፊት ነበር።) ዘፍጥረት 17:17፥ ኩፋሌ 12:32 እንደሚለን የአብርሃም ዕድሜ መቶ ሲሆን የሣራ ዕድሜ 90 ዓመት ስለ ተባለ ከአብርሃም በኋላ 10 ዓመታት እንደ ተወለደች ይመስላል። ዘፍጥረት 23:1 እስከ 127 ዓመት በሕይወት ኖረች ይለናል። በኩፋሌው ዜና መዋዕል መሠረት ግን ሣራ በ2024 ዓመተ ዓለም ዐረፈች ፣ ይህ ከአብርሃም ልደት 148 አመታት በኋላ ሊቆጠር ስለሚችል እነዚህ ቁጥሮች ሁሉ አይስማሙም። የሣራ ዕድሜ በዘፍጥረት 23:1 እስከ 138 ዓመት ድረስ ከሆነ ግን ሁላቸው ይስማሙ ነበር። በዕብራይስጥ ኦሪት ዘፍጥረት የተሠጡት ዕድሜዎች እንዲህ አይነት ልዩነት ስለሚበዛ፣ ይህ የአይሁድ ረቢዎች ቅጂዎች ግድፋት አልነበረም ለማለት አንችልም። ሦራ ከአብራም ጋራ ከዑር ወደ ካራን፣ ከካራንም ወደ ከነዓን ተጓዘች። አብርሃም የቤተሠቡ ባለቤት ሲሆን በከብትና በሎሌዎች ረገድ በጣም ሀብታም ሆነ። ረሃብ ወደ ከነዓን አገር በደረሰ ጊዜ ግን ወደ ግብጽ ሄዱ። የሣራህ ውበት ታዋቂ ነበረ፣ በዚያን ጊዜ የግብጽ ሰዎች ለራሳቸው እንዲይዟት ባሏንም አብርሃምን እንዲገድሉት የሚል ጭንቀት ለአብርሃም ነበረ። ስለዚህ እህቱ ብቻ እንደ ሆነች ለማለት አዘዛት። እንዲህ ሆነ፣ የግንጽም ፈርዖን ሣራን ወደ ቤተ መንግሥቱ ጨመራትና ለአብርሃም የብዙ ከብቶች ዋጋ ሰጠው። ሳይነካት ግን እግዚአብሔር ቤተ መንግሥቱን በመቅሠፍት መታ። ስለዚህ ፈርዖን በደሉን ስላወቀ አብርሃምን ሦራንና ከብቶቻቸውንም ከዚያ ሰደዳቸው። በኩፋሌ ዘንድ እነሱ በግብጽ ለ7 ዓመታት ቆዩ፣ ግብፃዊት ባሪያዋን ሀጋርን በዚህ ዘመን እንዳገኙ ይሆናል። ሣራ እስካሁን ድረስ መካን ሆና ልጅ እንዲገኝ ባሪያዋን ሀጋርን ለአብራም እንደ ሁለተኛ ሚስት ሰጠቻት (ዘፍጥረት 16:3)። ሀጋር የአብርሃም ሚስት ምንም ብትሆን ግን ለሣራ በባርነት ቆየች፣ ስለዚህ ርጉዝ ከሆነች በኋላ በሀጋርና በእመቤቷ በሣራ መካከል መቀኝነት መጣ። ሀጋር ለአብራም እስማይልን ወለደች። ከጥቂት ዓመታት በኋላ የሥላሴ 3 መላዕክት አብርሃምን በከነዓን ሲጎበኙ ሣራ እራሷ ልጅ እንድትወልድ አሉ። ሣራም በዕድሜዋ ልጅ እንድትወልድ ሰምታ በልብዋ ሳቀች። ለምን ሳቅሽ ሲላት ደግሞ አልሳቅሁም ብላ ካደችው። እግዚአብሔር ለኔ ምንም የማይቻለኝ ሥራ የለም አላቸው። ልክ እንዳላቸውም ሣራ ለአብርሃም ልጁን ይስሐቅ ወለደ። ከዚህ በኋላ ከእመቤቷ ጋር ስለ ነበረው መቀያየም ሀጋርና እስማይል ሸሽተው የእስማይል ልጆች በፋራን ምድረ በዳ ሠፈሩ። ሣራ ገና እርጉዝ በነበረችበት ወቅት በጌራራ ሲቆዩ፣ አብርሃም እንደገና እህቴ ብቻ ናት ብሎ አስመሰለ። እንደ ዘመኑ ልማድ የአገሩ ንጉሥ አቢሜሌክ ለራሱ እንድትሆን ወሰዳት። እንደገና ንጉሡ ሳይነካት እግዚአብሔር ማለደ፣ በሕልሙ ውስጥ ዛተው። የእግዜር ፈቃድ ከአቢሜሌክ ይልቅ አሸነፈና ያንጊዜ ሣራ በነጻ ወጣች፣ አቢሚሌክ ደግሞ ለአብርሃም ብዙ ከብትና ብር ጨመረ (ዘፍጥረት ምዕራፍ 20) ። ሣራ ቢያንስ 127 ዓመታት ሆና ባረፈችበት ዘመን አብርሃም ለመቃብር አንድ ዋሻ በኬብሮን ከኬጥያዊው ሰው ኤፍሮን ገዛ። ሣራ የታማኝነት አራያ ሆና በአዲስ ኪዳን ብዙ ጊዜ ትከበራለች -- ሮማውያን 4፡19፣ 9፡9፤ ዕብራውያን 11፡11፣ ወደ ገላትያ ሰዎች 4፡22-26፤ 1 ጴጥሮስ 3፡6። በቁርአን ደግሞ ሣራ በስሟ ባትጠቀስም በዘፍጥረት ከተገኘው ታሪክ ብዙ አይለይም። በኋላ የአይሁድ ረቢዎች (ከፈሪሳውያን ወገን የወጡ) እንደ ልማዳቸው ስለ ሣራ የጻፉት ተጨማሪ መረጃዎችና ትችቶች ብዙ አሉ። መጽሐፍ ቅዱስ የብሉይ ኪዳን ሰዎች
17742
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%89%B4%E1%8C%8C%20%E1%88%9D%E1%8A%95%E1%89%B5%E1%8B%8B%E1%89%A5
እቴጌ ምንትዋብ
እቴጌ ምንትዋብ በዙፋን ስሟ ብርሃን ሞገስ በ1698 ዓ.ም. ከአባቷ ደጅአዝማች መንበር እና እናቷ ልዕልት እንኮይ በቋራ፣ ጎንደር ስትወለድ የክርስትና ስሟ ወለተ ጊዮርጊስ ነበር። እናቷ ልዕልት እንኮይ ከዓፄ ሚናስ ዘር የምትወለድ እንደነበረች ይጠቀሳል። ምንትዋብ በ18ኛው ክፍልዘመን ኢትዮጵያ ላይ ብዙ አሻራ ትታ የለፈች ንቁ፣ ሃይለኛና ተራማጅ መሪ ነበረች። ከባሏ ዓፄ በካፋ ዘመን ጀምሮ እስከ ልጇ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ እና ልጅ ልጇ ዓፄ እዮዋስ ዘመን ድረስ ለ40 አመታት የአገሪቱ እኩል መሪ የነበረች ናት። በዚህች መሪ ዘመን በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ የህንጻዎች ግንባታና የቤተክርስቲያን ድረሰት፣ እንዲሁም ስነ ጥበብ እድገት ታይቷል። በፋሲል ግቢ የመጨረሻውን ግንብ ያስገነባችው ምንትዋብ ነበረች። ከልጆቿ የእድሜ አናሳነትና እራሷም በሰራቻቸው አንድ አንድ ስህተቶች ምክንያት በስልጣን በነበረችበት ዘመን የነበረው እድገትና ሰላም እርሷ ስታልፍ አብሮ አለፏል። እንግዴህ አገሪቱ ወደ ዘመነ መሳፍንት የተሻገረችው ልክ እርሷ እንዳለፈች ነበር። ዐፄ በካፋ ከዐፄ በካፋ ጋር ስለመገናኘቷ ዐፄ በካፋ በህዝብ ዘንድ ክብርን ካስገኘለት ስራው አንዱ ብዙ ጊዜውን በመሰዋት፣ እራሱን ደብቆ በግዛቱ ሁሉ እየተዘዋወረ ስህተት የተሰራውን ማቃናቱ ነበር። በዚህ ሁኔታ አንድ ቀን ተደብቆ ከጣና ሃይቅ በስተ ምዕራብ ሲጓዝ ቋራ ላይ ወባ ታመመና ከአንድ ገበሬ ቤት አረፈ። የስኮትላንዱ ተጓዥ ሐኪም ይጋቤ ሲተርክ "ወጣቷ ምንትዋብ ከመጠን በላይ ቆንጆ፣ ተግባቢና ልዝብ" የነበረች ሲሆን በካፋ ታሞ ያረፈበት ቤት ባለቤት ልጅ ነበረች። ምንትዋብ ታማሚውን ንጉሥ ተንክባክባ ለጤንነት ስላበቃችው ጳጉሜ5፣ 1716 (እ.ኤ.አ) ላይ ወደ ጎንደር ከተማእንዳስመጣትና እንዳገባት ይዘግባል። በ1717 ዳግማዊ አጼ ኢያሱን ወለደች። ከዚህ በኋላ ለ2 አመት ጎንደር ከተማ ተቀምጣ በመካከሉ በ1718 ወደ ወልቃይት እንድትሄድ ተደረገ። ምንም እንኳ ከሁለት ወር በኋላ ብትመለስም ልጇ ግን ወደ ሰሜን ሽሬ፣ ትግሬ ተልኮ በዚያ እስከ 1730 መኖር ቀጠለ። የአጼ በካፋ መሞትና የምንትዋብ መንገሥ አጼ በካፋ በ1722 ዓ.ም. ሲሞት የከተማው ህዝብ ሞቱን ሊቀበል አልቻለም። ለዚህ ምክንያቱ ከአሁን በፊት ንጉሱ ሳይሞት የሞተ በማስመሰል ህዝቡ ላይ ሽብር በመፍጠሩ ነበር። ምንትዋብም ባሏ ሲሞት የህዝቡን ጥርጣሬ በመጠቀም ውስጥ በማስገባትና ከቋራ አምስት ወንድሞቿ መጥተው የቤተመንግስት ስልጣን እስኪጨብጡና እስኪያረጋጉ ድረስ የንጉሱን ሞት ደብቃ ቆየች። ከወንድሞቿ መምጣት በኋላ እርሷና ዘመዶቿ ሆነው የ7 አመት ልጇን ኢያሱን ለማንገስ ቻሉ። ከ2 ወር በኋላ ታህሳስ 15፣ 1722 ላይ የልጇን ህጻን መሆን በማስታከክ እራሷ ላይ ዘውድ በመጫን በንግሥት ሥልጣን እንደራሴነቷን አሳወጀች። ለሚቀጥሉት 40 አመታት እርሷና ወንድሟ ወልደ ልዑል ከንጉሥ ልጇና ልጅ ልጇ ጋር እኩል ተሰሚነት ኑሯቸው አገሪቱን ለማስተዳደር በቁ፡፡ አንዳንዶች ይህ በዝምድና የተተበተበ አመራርና ያስከተለው የዘር ፉክክር አገሪቱን ለዘመነ መሳፍንት ያበቃ ተግባር ነበር ሲሉ ይታዘባሉ። የምንትዋብ አስተዳደር ምንትዋብና ልጇ ይከተሉት የነበረው ፖሊሲ ፊት ለፊት መጋፈጥ ሳይሆን እርቅንና መስማማትን ነበር። ለዚህ ተግባር እንዲረዳት፣ በጣም ቆንጆ የሚባሉ ሶስት ሴት ልጆቿን (ከበካፋ ሞት በኋላ ካገባችው ምልምል ኢያሱ የተወለዱ) በዘመኑ ኃይለኛ ለተባሉ የጎጥ መሪወች በመዳር (ወለተ እስራኤልን ለጎጃም ጦረኛ ደጃች ዮሴዴቅ ወልደ ሃቢብ ፣ ወይዘሮ አልጣሽን ለሰሜን ባላባት ወልደ ሃዋርያት (የራስ ሥዑል ሚካኤል ልጅ)1747 እና ወይዘሮ አስቴርን ለትግሬ መሪ ራስማርያም ባሪያው1761) በመዳር በግዛቷ ስላም አስፍና ነበር። ንግስቲቱ በማዕከላዊው መንግስት ሹም ሽረት ብታደርግም ራቅ ብለው የሚገኙት ክፍሎች ግን በራሳቸው እንዲተዳደሩ አድርጋ ነበር። የኦሮሞ ቡድኖች ወደ ሰሜን የሚያረጉትን ዘመቻ ስላቋረጡ በደቡብ በኩል መረጋጋት ተከስቶ ነበር። በሌላ ጎን፣ በደቡብ የተወሰዱ መሬቶችን ለማስመለስ ምንም አይነት ዘመቻ በዚህ ዘመን አልተካሄደም። ስለሆነም ከጊዜ ወደጊዜ ራቅ ያሉ ስፍራወች ኢ-ጥገኝነታቸው እየጎላ ሄደ። ከነበረው አጠቃላይ ሰላም አንጻር ልጇ እያሱ ወደ ሰሜን የሚያደርገው ዘመቻ የፖለቲካ ሳይሆን ለአደንና መሰል ክንውኖች ነበር። ምንትዋብና ያከናወነቻቸው ስራዎቿ በልጇና በልጅ ልጇ ዘመናት ለ40 ዓመት ስትነግስ ያከናወናቸቻው ስራወች ብዙ ነበሩ። ምንትዋብ በባህሪዋ ተራማጅና ንቁ ነበረች። በቤተክርስቲያን ተነስቶ በነበረው የቅባት እና ተዋህዶ ክርክር ለማስታረቅ ያደረገችው ጥረት የተሳካ ነበር። ስለሆነም ከሞላ ጎደል በአስተዳደሯ ወቅት ሃይማኖታዊ ስላም ነግሶ ነበር። ከሌሎች መንፈሳዊ ስራዎቿ ውስጥ ብዙ አብያተ-ክርስቲያናትንና ግንቦችን በማነጽ እንዲሁም በግሏ እየተከታተለች ድርሰቶችን በማስደረስ ስሟ ይጠቀሳል። ቁስቋምን በደብረ ፀሐይ ስለመመስረቷ እቴጌ ምንትዋብ በተለያዩ ምክንያቶች እራሷን ከጎንደር ከተማ ለማራቅ ጥረት አድርጋለች። የዚህ ጥረት ውጤት ከጎንደር ከተማ 3 ኪሎሜትር ራቅ ብሎ በሚገኘውደብረ ፀሐይ (ቁስቋም) ያሰራቻቸው ህንጻወች ናቸው። የስኮትላንድ ተጓዥጄምስ ብሩስ (ሃኪም ይጋቤ) በኒህ ህንጻወች አንድ ክፍል ተሰጥቶት ይኖር ነበርና ስለቁስቋም ሲጽፍ 3 ፎቅ የሆነ ቤተመንግስት፣ ክብ የሆነ ቤተክርስቲያንና ብዙ የተለያዩ የሰራተኞችና ዘበኞች ቤቶች እንዲሁም ግብዣ ቤት በአንድ ማይል ዙርያ በታጠረ ግቢ ይኖር እንደነበር አስፍሯል። እነዚህን ቤተመንግስቶችና ቤተክርስቲያኖች ከ1723 ጀምራ በማሰራት በ1732 ነበር ያስመረቀቻቸው። በግቢው ውስጥ የሚገኘው ቤተ ክርስቲያን፣ ደብረ ፀሐይ ማርያም ይባላል። በጄምስ ብሩስ ግምት፣ ኢትዮጵያ ከሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሃብታም የነበረና ብዙ ምርጥ ምስላትንና በወርቅና በብር የተሰሩ የቤተክርስቲያን መገልገያ ዕቃወችን የተመላ ነበር። የተገነባውም በአናጢዎችመሪ በጅሮንድ ኢሳያስ እና አዛዥ ማሞ፣ አዛዥ ህርያቆሳና አዛዥ ናቡተ መሪነት ነበር። ቤተክርስቲያኑ በቀይ ሃር አሸብርቆ በዙሪያው 380 መስታውቶች ተተክለውት ብርቅርቅታው ጎንደር ከተማ ድረስ ይታይ ነበር። ነገር ግን ቤተክርስቲያኑና ሌሎች በግቢው የነበሩ ህንጻወች በሱዳን ወራሪ መሃዲስቶች፣ በ1880 ተቃጠሉ። አሁን በጊቢው የሚገኘው ቤተክርስቲያን በዚህ ፍርስራሽ ላይ የተሰራ ነው። ጛርጋ ስላሴና ሌሎች ህንጻዎች ስለማሰራቷ የአቡነ እውስጣጢዎስን ቤተክርስቲያን ሐምሌ 1729 ላይ አሰርታ ለማስመረቅ ችላለች።ጣና ሃይቅ በሚገኘው ደጋ ደሴት እንዲሁ የራሷ የሆነ ቪላ የነበራት ሲሆን በዚሁ ደሴት ለቅዱስ እስጢፋኖስ መታሰቢያ ያሰራችውን ቤተ ክርስቲያን በ1739 ለማስመረቅ ችላለች። በተረፈም በርሷ ዘመን በስዕል ያጌጡ ድርሳናትና አጠቃላይ ስነ ጥበብ የሚበረታቱ ስለነበር ከዚሁ ዘመን የሚመነጩ የስነ ጥበብ ውጤቶች እጅግ ብዙ ናቸው። ኪነትን ስለማሳደጓ እና በዘመኗ ስለተፈጠረው የስነ ስዕል አብዮት ምንትዋብ እጅግ መንፈሳዊ ነበረች። ለዚህ ስትል ብዙ መንፈሳዊ ስራወችን በገንዘብ ትደጉም ነበር። ብዙ መጻህፍት በዚህ ዘመን ተጽፈዋል፣ ከአረብኛም ተተርጉመው ወደ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት የተሰራጩት ብዛት ስፍር ቁጥር የለውም። ለስነጥበብ ከነበራት ትኩረትና ከምታደርገው ድጎማ የተነሳ በዚሁ ዘመን በድንገት የተፈጠረ ልዩ አይነት የሥነ-ስዕል ስራ ተጀመረ። ይህ እንግዲህ በውጭ ሃገር የኪነት አጥኝወች ዘንድ ሁለተኛው የጎንደሪን የስነስዕል ስልት የሚባለው ነው። በአዲሱ ስልት ሥነ ሰዕል የቀጥተኛ መስመሮች ጥንቅር መሆኑ ቀርቶ በጎባጣ መስመሮች ጥንቅር የሚሰራና በህብረ ቀለማት የደመቀ ሆነ። የእውነተኛ ሰወች የሚመስሉ ምስሎችም መታየት ጀመሩ። በዚህ ሁኔታ በጣና ሃይቅ በአሰራችው ናርጋ ስላሴ ቤተክርስቲያን እና በቁስቋሙ ደብረፀሐይ ማርያም ግድግዳወች ላይ አይን የሚስቡ ምስሎች ተሰርተው ነበር። ሆኖም ብዙወቹ በመሃዲስት ሱዳኖች ሲወድሙ ንግስቲቱ በራሷ ክትትል ያስደረሰችው መጽሐፈ ራዕይ የትሰኘው በምስል ያሸበረቀ መጽሓፍ አሁን እንግሊዝ አገር ስለሚገኝ የአዲሱ የሥነ ሥዕል ስርዓት ቅርስ ከጥፋት ድኖ አሁን ቅርሱን መዝግቦ ይገኛል። በጊዜው ትታማባቸው የነበሩ ጉዳዮች አጼ በካፋ ከሞቱ በኋላ ከተወሰኑ ወንዶች ጋር ለአጫጭር ጊዜያት ትወጣ ነበር ተብላ ትታማ ነበር። በመጨረሻ፣ ምንም እንኳ ግራዝማች እያሱን ብታገባም የአማቷ ልጅ ከሞሆኑም በላይ ከእርሷ በድሜ ስለሚያንስ "ምልምል እያሱ" በሚል የሽሙጥ ስም ይታወቅ ነበር። ከዚህ ምልምል እያሱ 3 ሴት ልጆችን ስታተርፍ እነርሱም ልዕልት አስቴር፣ ልዕልት ወለተ እስራኤልና ልዕልት አልጣሽ ይባሉ ነበር። ። ልጇ ዐፄ እያሱ ይህን ምልማል እያሱን ይጠላው ነበር፤ ስለሆነም አንድ ቀን ለሽርሽር እንውጣ ብሎት ጣና ሃይቅ አካባቢ በአሽከሮቹ ተገፍትሮ ገደል ውስጥ እንዲሞት እንዳደረገ ይጠቀሳል። ታሪክ ፀሐፊው ተክለ ጻድቅ መኩርያ እንደዘገበ፣ ሺህ ነዋ የሚለው ቀልድ ከምንትዋብ የግብዣ አዳራሽ ነበር የፈለቀው። በተረፈ ንግስቲቱ በአንዱ ቅድም አያቷ ፖርቱጋላዊ ነበረች ተብላ ስለምትታማ ለካቶሊኮች ታደላለች የሚል ግንዛቤ በጊዜው ነበር ። የዘመነ መሳፍንት አጀማመር በኢትዮጵያ ታሪክ፣ በተደጋጋሚ እንደሚታየው፣ የህጻናት ስልጣን ላይ መውጣት አገሪቱን ከጥንት ጀምሮ ለውድቀት የዳረገ ነበር። የዳግማዊ አጼ ኢያሱና የልጁ የኢዮዋስ በህጻንነታቸው መንገስ ከዚሁ እውነታ የተለየ አልነበረም። አጼ በካፋ ሲሞት ልጁ ኢያሱ መንገሱ ህጋዊ ቢሆንም ህጻን ስለነበር ሃይል ለማግኘት የግዴታ ከሌላ ቦታ የፖለቲካ መሰረት ማግኘት ነበረበት። ስለሆነም እናቱ እቴጌ ምንትዋብ የምትተማመንባቸው የቋራ ዘመዶቿን በቤተ መንግስት ሾመች። ለምሳሌ፡ ወንድሟ ወልደ ልዑልን በራስ ማዕረግ። በዚህ ስራዋ ቀደምት በጎንደር ከትማ ስልጣን የነበራቸው ባላባቶች በጣም ጠሏት። ስለሆነም ከ1735-1736 እርሷንና ልጇን ከስልጣን ለማስወገድ ባላባቱ ሞከርው አመጹ ስለከሸፈ ይብሱኑ የቋራ ዘመዶቿን በከፍተኛ ስልጣንና በሰራዊቱ ላይ ሾመች ። ስልጣኗ እንዳይናጋ፣ የባላባቱን ኃይል በየጁወች ሃይል ለማጣፋት በማሰብ ልጇ አጼ ኢያሱን ለየጁ ባላባት ልጅ የሆነችውን ውቢት ( ክርስትና ከተነሳች በኋላ ወለተ ቤርሳቤሕ) ዳረች። ሆኖም ግን ንጉሱ ክርስቲያን ያልሆነች የየጁ ሴት አገባ ተብሎ ይታማ ስለነበር ጋብቻው በከተማው እርሱን ያስጠላና ድብቅ እንጂ በግልጽ የሚካሄድ አለነበረም። በመካከሉ ቤርሳቤሕ ቀስ በቀስ የየጁ ዘመዶቿን ልክ ምንትዋብ የቋራ ዘመዶቿን በቤተመንግስት እንደሰገሰገች ታደርግ ነበር። በዚህ ሁኔታ በየጁዎችና በቋራዎች የለሆሳስ ፉክክር ተጀመረ። ዳግማዊ አጼ ኢያሱ በ1747 ሲሞትና ከቤርሳቤሕ የወለደው ልጁ እዮዋስ ሲነግስ ምንትዋብ መልሳ እንደራሴነቷን አጸናች። ቤርሳቤሕ በበኩሏ ልክ ምንትዋብ የኢያሱ ሞግዚት እቴጌ እንደነበረች፣ እርሷ በተራዋ ለእዮዋስ እንደራሴነት(እቴጌነት) ይገባኛል በማለቷ በሁለቱ ጥል ተነሳ። በዚህ ወቅት አጼ እዮዋስ አያቱን ምንትዋብን ከመደገፍ ይልቅ የቤርሳቤህና የየጁዎች ወገን ሆነ። ውዝግቡ በ1759ዓ.ም. ወደ የርስ በርስ ጦርነት አመራ። በዚህ ጦርነት፣ የየጁም ሆነ የቋራ ክፍሎች ሃይላቸው ስለተዳከመ፣ ከትግሬ ገዢ ራስ ሥዑል ሚካኤል እገዛ ፈለጉ። ሥዑል ሚካኤል መጀመሪያ የንጉሱና የጁወች ደጋፊ የሆነ ቢሆንም በምንትዋብ የዲፖሎማሲ ስራ ኋላ የርሷ አጋር በመሆን አቋሙን ቀየረ። በስተመጨረሻ 1769 ላይ ሥዑል ሚካኤል፣ አጼ እዮዋስ የጁወችን በጦርነት ደግፏል በሚል ክስ እንዲገደል አደረገ። የንጉሱ መገደል በአገሪቱ ሲሰራበት የነበረውን ትውፊት የቀየረ እንግዳ ስራ ነበር። እንግዲህ እስከ ብዙ ዘመን ድረስ የነበረውን የንጉስ ክብር የነካ ስለነበር የሚፈራ አንድ ሃይል በመታጣቱ አገሪቱ ወደ ዘመነ መሳፍንት - ሁሉ በሁሉ ጦርነት ገባች። ምንትዋብ፣ ምንም እንኳ የየጁዎች ዋና ተቃዋሚ የነበርች ብትሆንም፣ የልጅ ልጇን መገደልና የሥዑል ሚካኤልን መግነን በመጥላት 1762 ላይ ወደ ጎጃም ሸሽታ ከሄደች በኋላ 1763 ተመልሳ ከጎንደር 3 ኪሎ ሜትር ሰሜን-ምዕራብ በሚገኘው ቁስቋም ባሰራችው ቤተ መንግስት ኑሮ ጀመረች። ከዚህ በኋላ ሃይሏ በመዳከሙ አገሪቱ ቀስ በቀስ እየተከፋፈለች ወደ ዘመነ መሳፍንት ስትሻገርና በስልጣን ትሥሥር ያስቀመጠቻቸው ዘመዶቿ ሲዋረዱ ከማየት በስተቀር ምንም ማድረግ አቅቷት ግንቦት ፳፮ ቀን ፲፯፻፷፭ ዓ/ም አረፈች። የእቴጌ ምንትዋብ ትውልድ =አቤቶ ዋክሶስ የቡላው| = ወይዘሮ ዮልያና}} ዋቢ መጻሕፍት ተክለጻድቅ መኩሪያ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ፡ ከዐፄ ልብነ ድንግል እስከ ዐፄ ቴዎድሮስ ፪/፪ ታሪክ ወንግሥት ብርሃን ሞገሳ - ወይንም - የእቴጌ ምንትዋብ ዜና መዋዕል ከዚሁ ዘመን የሚመነጩ ቀሪ ምስሎች መደብ :የኢትዮጵያ ታሪክ መደብ :ምንትዋብ
14392
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%88%E1%8A%95%E1%8C%8C%E1%88%8D
ወንጌል
ወንጌል የሚለው ቃል (ከላቲን / ኢቫንጄሊየም, ይህም ራሱ ከጥንት የግሪክ ቃል / ኧውጄሊዮን = አስደሳች መልዕክት) ከሚለው የተገኘ ቃል ነው። ወንጌል ለሰው ልጆች ሁሉ የሆነ መልካም የምሥራች ነው፡፡ የንስሐ፣ የመፍትሄ፣ የሰላም፣ የፍቅር፣ የተስፋ፣ የደኅንነት፣ የእርቅ፣ ከፍርድ የመዳን፣ የዘላለም ሕይወት፣ ትምህርት የሚገኝበት ቅዱስ መጽሐፍ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር መንግስት አዋጅ የሆነውን ወንጌል ለመጀመሪያ ጊዜ እሱ ራሱ እንደሰበከ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል (ማቴ.፬፡፳፫፣ ማርቆ.፩፡፲፬-፲፭)፡፡ የወንጌል ዋነኛው መልዕክት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኝ የኃጢአት ሥርየት ነው። ሰዎች ከእግዚአብሔር ቁጣ እንዲተርፉ፤ኃጢአት የሚያስከፍለውን ዋጋ ለመክፈል ማለት ከሁሉ የከፋውን ሞትን ለመሻር ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና ተወልዶ እንደ ሰው ሆኖ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ ከሞት መነሣቱን በፈቃደኝንት ማለትም በሰላማዊ መንገድ አምኖ ማሳመን ነው (ሐዋ.፲፫፡፳፰-፴፣፴፰። ሮሜ.፫፡፳፭-፳፮፣ 1ቆሮ.፲፭፡፫-፬)። በተለይ የዘላለማዊ ሕይወት ዕጣዬ ምንዓይነት ነው ለሚለው ጥያቄ ወንጌል ግልፅ የሆነ መልስ ይሰጣል። የወንጌል ዋና መልእክት የወንጌል አንኳር መልዕክት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኝ የኃጢአት ሥርየት ነው። የድኅነት ሥራ በክርስቶስ ተፈፅሟል የአዋጁ ዋና መልዕክት ነው (ሐዋ.፪፡፴፰፣ ፭፡፴፩፣ ፲፡፵፫፣ ፲፫፡፴፰፣ ፳፮፡፲፰) ። የድኅነት ስራ በክርስቶስ ኢየሱስ ስለተከናወነ፣ ሰዎች በእርሱ እንዲያምኑ እና የዘላለምን ህይወት እንዲያገኙ የሚነገር የምስራች ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደተናገረው ወንጌል በመስቀል ላይ የተከናወነውን አስደናቂ የድኅነት ስራ የማወጅ ተግባር ነው፣ “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ..” (፩ኛቆሮ.፲፭፡፩-፬)። የክርስቶስ ሞት እና ትንሳዔ የወንጌል ማዕከል ነው። ወንጌል ለፍጥረት ሁሉ የሚታወጅ የመስቀሉ የማዳን ሥራ ነው፣ “ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው…” (፩ኛ.ጢሞ.፩፡፲፭)። ወንጌል ሰዎች ከኃጢአታቸው ንስሃ በመግባት የበደላቸውን ስርየት እንዲቀበሉ ይናገራል፣ “..በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል” (ሉቃ.፳፬፡፵፯) ። በወንጌል የተገኘው ደኅንነት የሰው ልጅ በመስቀል ላይ በተሰራው የድኅነት ሥራ በማመን የኃጢአት ሥርየትን ያገኛል፣ ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ይታረቃል፣ እንደ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል፣ የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ መንግስት ይወርሳል ከእግዚአብሔር ጋር ወደ ቀደመው የፍቅር ህብረት ይመለሳል በዚህ ዓለም ሲኖር የዘላለማዊ ተስፋ ያገኛል የምሥራቹን ወንጌል የማወጅ መብትና ብቃትን ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል በኃጢአት ምንክንያት ከሚመጣ የእግዚአብሔር ፍርድ ይድናል ኢየሱስ ከሰበካቸው “ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከና ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ” (ማርቆ.፩፡፲፬-፲፭)። መጽሐፍ እንደሚል “በልጁ የሚያምን የዘላለም ህይወት አለው” (ዮሐ.፫፡፴፮)። በኃጢአት ምክንያት ከሚመጣ የዘላለምም ፍርድ ያመልጣል፣ “በእርሱ የሚያምን አይፈረድበትም..”(ዮሐ.፫፡፲፰)። ይሄንን የድኸነት ወንጌል ሐዋርያትም ሰብከውታል፣ “ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ” (ሐዋ.፪፡፴፰)። የጥንት የቤተክርስቲያን አባቶችም ሰብከውታል። ወንጌል በእስልምና “ወንጌል” የሚለው የግሪኩ ቃል “አንጀሊኦን” ሲሆን “የምስራች” አሊያም “መልካም ዜና” የሚል ፍቺ አለው፣ “ኢንጂል” የሚለው የአረቢኛው ቃል “ኢወንጀሊየን” ከሚለው አረማይክ ቃል አቻ ሲሆን ትርጉሙ በተመሳሳይ “የምስራች” ማለት ነው፣ “ኢንጂል” የሚለው ቃል በቁርአን 12 ጊዜ ተጠቅሶ ይገኛል፤ ይህም ወንጌል ለኢሳ የተሰጠው ወህይ ነው፦ 19:30 ሕፃኑም አለ እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፤ መጽሐፍም *”ሰጥቶኛል”* ነቢይም አድረጎኛል። 57:27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን የመርየምን ልጅ ኢሳንም አስከተልን፤ *”ኢንጅልንም ሰጠነው”*፤ 5:46 *”ኢንጂልንም”* በውስጡ ቀጥታና ብርሃን ያለበት በስተፊቱ ያለችውን ተውራትንም የሚያረጋግጥ ለጥንቁቆችም መሪና ገሣጭ ሲሆን *”ሰጠነው”*። ኢየሱስ ከራሱ ሳይሆን የላከው የሰጠውን ቃል እንደሚናገር እንጂ ከራሱ ምንም ሳይናገር ያ የተሰጠውን ቃል ለሃዋርያት እንደሳጣቸው ይናገራል፦ ዮሐንስ 12:49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ *”የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ”*። ዮሐንስ 17:8 *”የሰጠኸኝን ቃል”* ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ይህም የተሰጠው ቃል የላከው የፈጣሪ ንግግር ነው፦ ዮሐንስ 17:14 እኔ *”””ቃልህን””* ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔም ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉምና ዓለም ጠላቸው።” ዮሐንስ 14:24 የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል *””””የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም”””*። ዮሐንስ 7፥16 ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። *”ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም”*፤ ምክንያቱም ኢየሱስ ሲያስተምር የነበረው ከፈጣሪ እየሰማ ነበር፦ ዮሐንስ 8.40 ነገር ግን አሁን *”ከእግዚአብሔር የሰማሁትን”* እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤ ዮሐንስ 8.26 ዳሩ ግን የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም *”ከእርሱ የሰማሁትን”* ይህን ለዓለም እናገራለሁ አላቸው። ዮሐንስ 5:30 እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ *”እንደ ሰማሁ”* እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና። ዮሐንስ 15:15 ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፥ *”ከአባቴ የሰማሁትን”* ሁሉ ለእናንተ አስታውቄአችኋለሁና።” ዮሐንስ 12:50 ትእዛዙም የዘላለም ሕይወት እንደ ሆነች አውቃለሁ። ስለዚህ *”እኔ የምናገረውን አብ እንደ ነገረኝ እንዲሁ እናገራለሁ”*። እግዚአብሔር ኢየሱስ የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ ይህም ቃል የእግዚአብሔር ወንጌል ነው፤ ሕዝቡም የሚሰሙት የእግዚአብሔር ቃል ነበረ፦ ዮሐንስ 3፥34 እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ ሉቃስ5፥1 ሕዝቡም የእግዚአብሔርን ቃል እየሰሙ ሲያስጠብቡት ሳሉ፥ እርሱ ራሱ በጌንሳሬጥ ባሕር ዳር ቆሞ ነበር፤ “ነብይ” ማለት በዕብራይስጥ “ተናጋሪ” ወይም “ነጋሪ” ማለት ነው፤ ነብይ ማለት የሌላ ማንነት ንግግር ተቀብሎ የሚያስተላልፍ “አፈ-ቀላጤ” ወይም “ቃል አቀባይ” ማለት ነው፤ በዚህ ስሌት ኢየሱስ ከአምላክ ሰምቶ የሚያስተላልፍ ነብይ ነው፦ ዘኍልቍ 12:6 እርሱም። ቃሌን ስሙ፤ በመካከላችሁ *“ነቢይ”* ቢኖር፥ እኔ እግዚአብሔር “በራእይ” እገለጥለታለሁ፥ ወይም “በሕልም” እናገረዋለሁ። ማቴዎስ 21፥11 ሕዝቡም። ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ *”ነቢዩ ኢየሱስ ነው”* አሉ።” ሉቃስ 24፥19 እርሱም። ይህ ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱም እንዲህ አሉት። *በእግዚአብሔርና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ ነው”* ። ማርቆስ 6፥4 ኢየሱስም። *ነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ዘመዶቹ ከገዛ ቤቱም በቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው*።” ታዲያ ከፈጣሪ ተሰጦት ሲያስተላልፍ የነበረው ቃል ምንድን ነው? ካልን ወንጌል ነው፤ ኢየሱስ ሲናገረው የነበረው ወንጌል እንደነበር ይናገራል፦ ሉቃ 4:17 የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች *ወንጌልን እሰብክ* ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ሉቃ4:43 እርሱ ግን። ስለዚህ *ተልኬአለሁና ለሌሎቹ ከተማዎች ደግሞ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እሰብክ ዘንድ ይገባኛል* አላቸው። ማቴዎስ 4:23 ኢየሱስም በምኩራቦቻቸው እያስተማረ የመንግሥትንም *ወንጌል እየሰበከ* በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ በገሊላ ሁሉ ይዞር ነበር። ማቴዎስ 9:35 ኢየሱስም በምኩራቦቻቸው *እያስተማረ፥ የመንግሥትንም ወንጌል እየሰበከ*፥ በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ፥ በከተማዎችና በመንደሮች ሁሉ ይዞር ነበር። ማርቆስ 1:14 ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን *ወንጌል እየሰበከና*። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ *በወንጌልም እመኑ* እያለ ወደ ገሊላ መጣ። ኢየሱስ *”በወንጌል እመኑ”* ያለው የማቴዎስን፣ የማርቆስን፣ የሉቃስን፣ እና የዮሐንስን ትረካ ሳይሆን ከአላህ እንዲናገር የተሰጠውን መልእክት ነው፤ ኢየሱስ ከፈጣሪው ተሰጦት ሲናገር የነበረውን ወንጌል እኛ ሙስሊሞች እናምንበታለን። ወንጌል የኢየሱስ ወንጌል ብቻ ነው፤ የኢየሱስ ወንጌል የሚጀምረው ማስተማር ከጀመረበት ጊዜ ነው፤ ማስተማር የጀመረው በሰላሳ አመቱ ነው፦ ማርቆስ 1፥1 *”የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ”* ማርቆስ 1:14 ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን *ወንጌል እየሰበከና*። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ *በወንጌልም እመኑ* እያለ ወደ ገሊላ መጣ። ሉቃስ 3:23 *”ኢየሱስም ሊያስተምር ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ሆኖት ነበር”* ፤ ማስታወሻ፦ “ማርቆስ 1፥1 ላይ *የእግዚአብሔር ልጅ* የሚለው የግሪኩ ቀዳማይ እደ-ክታባት ላይ የለም” ከማስተማሩ በፊት ስለ ውልደቱ እና ተልእኮውን ከጨረሰ በኃላ ስለ እርገቱ የሚያወሩት የአራቱ ወንጌላት ክፍሎች ወንጌል ሳይሆኑ በኢየሱስ ወንጌል ላይ የተጨመሩ *”የታሪክ መዝገብ”* ወይም “የትውልድ መጽሐፍ” ነው፦ ማቴዎስ 1፥1 የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ *”የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ”* ። ሉቃ1:1-4 የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት *እንዳስተላለፉልን*፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር *”ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ”*፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው *”ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ”*። አላህ ከእርሱ የወረውን ይህንን እውነት በሰው ትምህርት ቅጥፈት እንደቀላቀሉት ይናገራል፦ 3:71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! *”እዉነቱን በዉሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ?”* እውንትም እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ? “እውነት” የተባለው ከአላህ የወረደው ቃሉ ነው፦ 34:48 ፦ጌታዬ *“እውነትን ያወርዳል”*፤ ሩቅ የኾኑትን ሚስጢሮች ሁሉ ዐዋቂ ነው በላቸው። “ውሸት” የተባለው ደግሞ መጽሐፉን በእጆቻቸው ፅፈው “ይህ ከአላህ ዘንድ ነው” ብለው የቀጠፉት ጭማሬ ነው፦ 2:79 ለነዚያም *”መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉ እና ከዚያም በእርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው”*፡፡ ለእነርሱም ከዚያ *”እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው”*፡፡ ለእነሱም ከዚያ ከሚያፈሩት ኃጢኣት ወዮላቸው፡፡ ስለዚህ ለኢየሱስ የተሰጠው የመጀመሪያው ወንጌል ከሰዎች ቃል ጋር ተበርዟል፤ ከላም የታለበ ወተት በብርጭቆ ተቀምጦ ሳለ በቡና ቢቀላቅሉት የመጀመሪያው ስረ-መሰረት ስለሌለ ሙሉ ወተት ሳይሆን ማኪያቶ ይባላል፤ ከላሟ የታለበው ወተት የት ገባ? ብትባሉ መልሳችሁ ምንድን ነው መልሳችሁ ተበርዟል ነው፤ ማክያቶ ውስጥ ወተት የለም እንዴ? ብትባሉ መልሳችሁ ምንድን ነው? በቅሪት ደረጃ አለ፤ በተመሳሳይም ከአላህ ለኢየሱስ የተሰጠው ወንጌል ሳለ በሰው ቃል ቢቀላቅሉት የመጀመሪያው ስረ-መሰረት ስለሌለ ሙሉ ወንጌል ሳይሆን ብርዝ ይባላል፤ ከአላህ ለኢየሱስ የተሰጠው ወንጌል የት ገባ? ብትባሉ መልሳችሁ ምንድን ነው? መልሳችሁ ተበርዟል ነው፤ የመጸሐፉ ሰዎች ውስጥ የወንጌል ቅሪት የለም እንዴ? ብትባሉ መልሳችሁ ምንድን ነው? በቅሪት ደረጃ አለ ነው፤ ያንን በቁርአን መዝነን እንቀበለዋለን፤ ቁርአን ያንን እነርሱ ጋር ያለውን መለኮታዊ ቅሪት ሊያረጋግጥ ወርዷል፦ 4:47 እላንተ መጽሐፉ የተሰጣችሁ ሆይ! .. *”ከእናንተ ጋር ያለውን የሚያረጋግጥ”* ኾኖ ባወረድነው ቁርአን እመኑ፣ 2:41 *”ከእናንተ ጋር ያለውን የሚያረጋግጥ”* ሆኖ ባወረድኩትም ቁርአን እመኑ፡፡ የመጽሐፉ ሰዎች ጋር ያሉት ቃላት ሙሉ ለሙሉ እውነትን ነው ብለን እንደማናምን ሁሉ ሙሉ ለሙሉ ሐሰት ነው ብለን አናምንም፤ ቁርአን ከወረደበት ግብና አላማ፣ ፋይዳና ሚና አንዱ ከእነርሱ ጋር ያለውን እውነት ለማረጋገጥና ቀጥፈው የጨመሩትን ሐሰት ሊያርም ነው፤ ከእነርሱ ጋር ያለውን እውነትን ስለሚያረጋግጥ “ሙሰዲቃን” “አረጋጋጭ” ሲባል፤ የሰዎች ንግግሮች የገቡበትን በማረሙ ደግሞ “ሙሃይሚን” “አራሚ” ” ወይም “ተቆጣጣሪ”” የሚል ስም አለው፦ 5:48 ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ *”አረጋጋጭ”* እና በእርሱ ላይ *”ተጠባባቂ”* ሲሆን በእውነት አወረድን፤ ሰዎች በወንጌሉ ላይ መጨምራቸው ብቻ ሳይሆን በመደበቅ የቀነሱትም ነገር አለ፤ በ 397 የተደረገው የካርቴጅ ጉባኤ ብዙ የወንጌል ቅሪት አፓክራፋ ብሎ ቀንሷል፤ “አፓክራፋ” ማለት “አፓክራፎስ” ከሚለው የግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን “ድብቅ” “ስውር” ማለት ነው፦ 5፥15 የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! *”ከመጽሐፉ ትሸሽጉት ከነበራችሁት ነገር ብዙውን ለእናንተ የሚገልጽ ከብዙውም የሚተው”* ሲኾን መልክተኛችን በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ ከአላህ ዘንድ ብርሃንና ገላጭ መጽሐፍ በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ 2፥146 እነዚያ መጽሐፍን የሰጠናቸው ወንዶች ልጆቻቸውን እንደሚያውቁ ያውቁታል፡፡ ከእነሱም የተለዩ ክፍሎች እነርሱ የሚያወቁ ሲኾኑ *”እውነቱን በእርግጥ ይደብቃሉ”* ፡፡ ከተደበቁት ዋናው አጀንዳ የምስራቹን የምስራች ያሰኘው ኢየሱስ ስለ ነብያችን መምጣት ማብሰሩ ነው፤ አላህ ኢንጅል የሚለው ስለ ነብያችን መምጣት የሚተነብየውን ወንጌል እንደሆነ ቅቡልና እሙን ነው፦ 61፥6 የመርየም ልጅ ዒሳም፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! እኔ ከተውራት በፊቴ ያለውን የማረጋግጥ እና *”ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልክተኛ ስሙ አሕመድ በኾነው የማበስር”* ስኾን ወደ እናንተ የተላክሁ የአላህ መልክተኛ ነኝ» ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ በግልጽ ተዓምራቶች በመጣቸውም ጊዜ «ይህ ግልጽ ድግምት ነው» አሉ፡፡ 7፥157 ለእነዚያ ያንን እነርሱ ዘንድ *”በተውራትና በኢንጂል ተጽፎ የሚያገኙትን የማይጽፍና የማያነብ ነቢይ”* የኾነውን መልክተኛ የሚከተሉ ለኾኑት በእርግጥ እጽፍለታለሁ፡፡
47199
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%AE%E1%88%9B%20%E1%8A%AB%E1%89%B6%E1%88%8A%E1%8A%AD%20%E1%89%A4%E1%89%B0%20%E1%8A%AD%E1%88%AD%E1%88%B5%E1%89%B2%E1%8B%AB%E1%8A%95
የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን
የካቶሊክ እምነት እውነተኛ መነሻ በክርስትና ታሪክ ስለ ካቶሊክ መነሻ እና የክርስትና መከፋፈል በስፋት ማወቅ ከፈለጉ ይህንን ጽሑፍ በእርጋታ ያንብቡ! አውጣኪ፣ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ እና የኬልቄዶን ጉባኤ በቀሲስ ዶ/ር ምክረ ሥላሴ ገ/አማኑኤል ከክርስቶስ ልደት በኋላ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ በመካከለኛው ምሥራቅ በተለይ በአንጾኪያና በግብጽ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ያወከና ታላቅ ብጥብጥ የፈጠረ በምሥጢረ ሥላሴ እምነት ላይ የተነሣ የተሳሳተ ትምህርት ነበር፡፡ ይኸውም አርዮስ ከእስክንድርያዊው መምህሩ ከአርጌኒስ በቀሰመው ትምህርት በዘዴ ‹‹ክብር ምስጋና ይግባውና እግዚአብሔር ወልድን ፍጡር ነው፤ አምላክም አይደለም፤›› ለማለት ‹‹ሀሎ አመ ኢሃሎ ወልድ›› (ወልድ ያልነበረበት ጊዜ ነበር) በግሪክኛ፡- ‹‹ኢን ፖቴ ኦቴ ኡክ ኢን›› ብሎ የክሕደት ትምህርት በማስተማሩ መላው የክርስትናው ዓለም ታውኮ ነበር፡፡ ይህ በ325 ዓ.ም. በኒቂያ ጉባኤ አርዮስና ኑፋቄው በመወገዙ ችግሩ መፍትሔ አግኝቶ ነበር፡፡ ከ106 ዓመታት በኋላ ደግሞ ንስጥሮስ ከአንጾኪያ በአገኘው ትምህርት በቊስጥንጥንያ ቤተ ክርስቲያን በምሥጢረ ሥጋዌ እምነት ላይ ስለ ክርስቶስ የተሳሳተ ትምህርት ያስተምር ጀመር፡፡ ይኸውም ንስጥሮስ 1ኛ ክርስቶስ ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ አለው፤ 2ኛ/ ክርስቶስ ፍጹም ሰው እንጂ ፍጹም አምላክ አይደለም፤ እንዲሁም 3ኛ/ እመቤታችን ሰውን እንጂ አምላክን አልወለደችም፤ ስለዚህ እመቤታችን ወላዲተ ሰብእ እንጂ ወላዲተ አምላክ ልትባል አይገባትም (ሕስወኬ ትሰመይ ወላዲተ አምላክ፣ በአማን ትሰመይ ወላዲተ ሰብእ) ብሎ በማስተማሩ ይህ ኑፋቄ በ431 ዓ.ም. ላይ በታላቁ መምህር በእስክንድርያው ፓትርያርክ በቅዱስ ቄርሎስ አማካኝነት በኤፌሶን ጉባኤ ተወግዞ ችግሩ ተወግዶ ነበር፡፡ ሆኖም የንስጥሮስ የክህደት እምነት ጨርሶ ሳይጠፋ በዚያው በመካከ ለኛው ምሥራቅ በተለይ በፋርስና በባቢሎን እንዲሁም በኤዴሳ ሲስፋፋ ቆይቷል፡፡ እንዲሁም ንስጥሮሳውያን በኤፌሶንና በቊስጥንጥንያ በብዛት ይገኙ ነበር፡፡ አውጣኪና ትምህርቱ የንስጥሮስን ትምህርት በጥብቅ ይቃወሙ የነበሩት የግብጽ መነኰሳትና ካህናት ነበሩ፡፡ በቊስጥንጥንያም ቢሆን አያሌ የንስጥሮስ ተቃዋሚዎች ነበሩ፡፡ የንስጥሮስን ትምህርት አጥብቆ ይቃወም የነበረና ለኦርቶዶክስ ሃይማኖት እጅግ ቀናኢ የነበረ አውጣኪ የተባለ በቊስጥንጥንያ የአንድ ትልቅ ገዳም አበምኔት (መምህር) ነበር፡፡ አውጣኪ ‹‹ክርስቶስ ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ አለው›› የሚለውን የንስጥሮሳውያንን ትምህርት አጥብቆ በመቃወም እሱ ወደ ተቃራኒው የባሰ ክህደት ውስጥ ገባ፡፡ አውጣኪ በቊስጥንጥንያ ‹‹ክርስቶስ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ብቻ አለው፤›› እያለ ያስተምር ጀመር፡፡ አባባሉ የቅዱስ ቄርሎስን ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት ይመስላል፡፡ አውጣኪ ግን ‹‹አንድ ባሕርይ›› ሲል የክርስቶስን መለኮታዊ ባሕርይ ብቻ ማለቱ ነበር፡፡ በአውጣኪ አባባል ‹‹ሁለቱ ባሕርያት ማለት የሥጋና የመለኮት ባሕርያት በተዋሐዱ ጊዜ የመለኮት ባሕርይ የሥጋን ባሕርይ ውጦታል፤ አጥፍቶታል፡፡ ሥጋና መለኮት ከተዋሐዱ በኋላ በክርስቶስ ላይ የሚታየው የመለኮት ባሕርይ ብቻ ነው፡፡ በክርስቶስ የሥጋ ባሕርይ ተውጦ የመለኮት ባሕርይ ብቻ ነው የሚታየው፤›› ይል ነበር፡፡ ይህ አባባል በእኛም ቤተ ክርስቲያን ማለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተወገዘ ነው፡፡ አውጣኪ በተጨማሪ ከሥጋዌ በኋላ ክርስቶስ ፍጹም ሰው ነው ለማለት ‹‹ክርስቶስ ዘዕሩይ ምስሌነ በትስብእቱ›› ማለት ‹‹ክርስቶስ በትስብእቱ (በሥጋው) ከእኛ ጋር አንድ ነው›› የሚለውን ኦርቶዶክሳዊ አነጋገር አይቀበልም ነበር፡፡ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት መሠረት ‹‹ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ነው፡፡›› ነገር ግን ፍጹም ሰው ካልሆነና እኛን ወክሎ በመስቀል ላይ በሥጋው መከራን ካልተቀበለ፣ የእኛ የሰዎች ድኅነት አስተማማኝ አይሆንም፡፡ በክርስቶስ የሥጋና የመለኮት ባሕርያት ተዋሕደው በመስቀል ላይ በአንድነት ባሕርዩ በተቀበለው መከራ ድኅነትን አግኝተናል፡፡ ‹‹በክርስቶስ የሥጋ ባሕርይ ተውጦ ወይም ጠፍቶ የመለኮት ባሕርይ ብቻ ነው የሚታየው›› የሚለውን የአውጣኪን የኑፋቄ (የክህደት) ትምህርት የሰማው የቊስጥንጥንያ ፓትርያርክ ፍላብያኖስ ወዲያውኑ ደብዳቤ ጽፎ ስሕተቱን በማስረዳት አውጣኪ ከስሕተቱ እንዲታረምና ይህን ትምህርት እንዳያሰራጭ አስጠነ ቀቀው፡፡ አውጣኪ ግን የኑፋቄ ትምህርቱን አላቆመም፡፡ ከዚህ ላይ አንድ ነገር ማስታወስ አለብን፤ ይኸውም አውጣኪ ክሪሳፍዮስ ለተባለው ለንጉሠ ነገሥቱ ለዳግማዊ ቴዎዶስዮስ ኃይለኛ ጠቅላይ ሚኒስትር የንስሓ አባት ስለነበር የልብ-ልብ የተሰማው ይመስላል፡፡ ፓትርያርክ ፍላብያኖስም ይህንን ስለሚያውቅ ይመስላል አውጣኪን በጣም ሊጫነው አልፈለገም፡፡ ሆኖም ኃይለኛ የነበረ የዶሪሊያም ሊቀ ጳጳስ የነበረው አውሳብዮስ አውጣኪን አጥብቆ ስለ ተቃወመውና ስለ ከሰሰው፣ የቊስጥንጥንያው ፓትርያርክ ፍላብያኖስ እንደተለመደው የመላው አብያተ ክርስቲያናት ጳጳሳት ተጠርተው ጉባኤ በማድረግ ፈንታ፣ በእርሱ ስር የሚተዳደሩትን ሃያ ዘጠኝ ጳጳሳትንና ሠላሳ ሦስት የገዳማት አበምኔቶችን ብቻ ሰብስቦ በእርሱ ሰብሳቢነት በ448 ዓ.ም. በቊስጥንጥንያ አህጉራዊ ሲኖዶስ አድርጎ የአውጣኪን የክሕደት ትምህርት መመርመር ጀመረ፡፡ አውጣኪ በጉባኤው ላይ እንዲቀርብ ሁለት ጊዜ ተጠርቶ ለመቅረብ አልፈለገም፡፡ ለሦስተኛ ጊዜ ሲጠራ ብቻ ቀርቦ ስለ ኑፋቄ ትምህርቱ ሲጠየቅ ግልጽ ያልሆነ የሃይማኖት መግለጫ በጽሑፍ አቀረበ፡፡ መግለጫው ግን ስለተከሰሰበት የክህደት ትምህርት ምንም አይገልጥም፡፡ ሆኖም የዶሪሊያም ጳጳስ አውሳብዮስ ግልጥ አድርጎ ‹‹ክርስቶስ በትስብእቱ ከእኛ ጋር አንድ ነው?›› ብሎ በጠየቀው ጊዜ አውጣኪ አንድ አይደለም በማለት ካደ፡፡ ከክህደቱም እንዲመለስ ቢጠየቅ አሻፈረኝ አለ፡፡ ስለዚህ ጉባኤው አውጣኪን አወገዘው፡፡ ከአበምኔት ሹመቱና ከክህነት ሥልጣኑም ሽሮ ተራ ሰው አደረገው፡፡ የሮሙ ፖፕ ለቊስጥንጥንያው ፓትርያርክ ፍላብያኖስ ‹‹ክርስቶስ ሁለት ባሕርያት አንድ አካል አለው›› የሚል የሃይማኖት ፎርሙላ የያዘ ደብዳቤ ልኮለት ስለነበረ፤ አውጣኪ ይህንንም ነበር እንዲቀበል የተጠየቀው፡፡ ይህ ደግሞ ከንስጥሮስ ኑፋቄ ጋር የተዛመደ ስለነበረ (ይህ አባባል መንፈቀ ንስጥሮሳዊ ይባላል) አውጣኪ አልቀበልም አለ፡፡ ስለዚህ አውጣኪ ‹‹የቅዱስ ቄርሎስን ሃይማኖት ስለመሰ ከርኩ እንጂ አንዳች የሃይማኖት ስሕተት ሳይኖርብኝ ያለ አግባብ ተወገዝኩ፤›› ብሎ ለንጉሠ ነገሥቱ ለዳግማዊ ቴዎዶስዮስ አመለከተ፡፡ እንዲሁም ለሮም ፖፕ ለልዮን ቀዳማዊና ለእስክን ድርያው መንበረ ፓትርያርክ ለዲዮስቆሮስ ለሌሎችም ጳጳሳት ደብዳቤ ላከ፡፡ የቊስጥንጥንያው ፓትርያርክ ፍላብያኖስም በበኩሉ የአውጣኪን ኑፋቄና ጉባኤው ስለ እርሱ የወሰነውን ውሳኔ ለፖፕ ልዮን ላከለት፡፡ ፖፑም የጉባኤውን ውሳኔ በማጽደቅ ምሥጢረ ሥጋዌን የያዘ ደብዳቤ ለፍላብያኖስ በድጋሚ ላከለት፡፡ በደብዳቤውም ውስጥ ክርስቶስ ሁለት ባሕርያትና አንድ አካል እንዳለው በግልጽ አስፍሯል፡፡ ይህም አባባል ከላይ እንደተገለጸው መንፈቀ ንስጥሮሳዊ ነው፡፡ ሁለተኛው የኤፌሶን ሲኖዶስ አውጣኪ በቊስጥንጥንያ እጅግ የተከበረ ሰው ስለነበረና ብዙም ደጋፊዎች ስለነበሩት የእርሱ በ448 ዓ.ም. ጉባኤ መወገዝ ብዙዎችን አስቆጥቶ ነበር፡፡ እንደውም ያወገዘው ፓትርያርክ ፍላብያኖስ ንስጥሮሳዊ ነው እየተባለ ይወራና ይወቀስ ጀመር፡፡ ንጉሠ ነገሥቱም የነገሩን ክብደት ተመልክቶ ምናልባትም በአውጣኪ ንስሓ-ልጅ በጠቅላይ ምኒስትሩ ተጽእኖ ይሆናል ዓለም-አቀፍ የአብያተ ክርስቲያናት ጳጳሳት ሲኖዶስ በኤፌሶን እንዲደረግ ለጳጳሳቱ ሁሉ ጥሪ አስተላለፈ፡፡ ስብሰባውም በነሐሴ ወር 449 ዓ.ም. በኤፌሶን እንዲሆን ተወሰነ፡፡ ባለፉት ሲኖዶሶች እንደተደረገው ሁሉ የእስክንድርያው ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ሰብሳቢ እንዲሆን ንጉሠ ነገሥቱ ወሰነ፡፡ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ሰብሳቢ በመሆኑ ሃያ ሦስት ከሚሆኑ ከግብጽ ጳጳሳት ጋር ቀደም ብሎ ኤፌሶን ደረሰ፡፡ ፖፕ ልዮን ግን ይህ ስብሰባ እንዲደረግ አልፈለገም ነበር፡፡ እንደውም ለንጉሠ ነገሥቱ ታላቅ እኅት ለብርክልያ ንጉሡ ጉባኤውን እንዳይጠራ እንድታግባባው ጠይቋት ነበር፡፡ ሆኖም ንጉሠ ነገሥቱ በሐሳቡ ጸንቶ ጉባኤውን ስለጠራ ፖፑም ሦስት መልእክተኞች ላከ፡፡ በጉባኤው ላይ አንድ መቶ ሠላሳ አምስት ጳጳሳት ተሰብስበው ነበር፡፡ ምንም እንኳ ጉባኤው ስብሰባውን የጀመረው አንድ ሳምንት ዘግይቶ ቢሆንም የሮሙ ፖፕ እንደራሴዎች በዚህ ጊዜ ሊገኙ አልቻሉም፡፡ የቊስጥንጥንያው ፓትርያርክ ፍላብያኖስም በጉባኤው ላይ እንዲገኝ ተጠርቶ አልመጣም፡፡ የቀረበትንም ምክንያት አልገለጠም፡፡ ምናልባትም በእሱ ሰብሳቢነት የተሰበሰበው አህጉራዊ ሲኖዶስ ያወገዘው የአውጣኪ ጉዳይ እንደገና እንዲታይ በመደረጉ ቅር ብሎት ሳይሆን አይቀርም፡፡ ይህ ደግሞ አዲስ ነገር አልነበረም፡፡ ከዚህ በፊትም ብዙ መናፍቃን አርዮስም ጭምር መጀመሪያ በአህጉራዊ ሲኖዶሶች ከተወገዙ በኋላ ነበር ጉዳያቸው እንደገና በዓለም-አቀፍ ሲኖዶሶች እንዲታዩ የተደረገው፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ጳጳሳት ተጠብቀው ባይመጡም ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ የተገኙትን አንድ መቶ ሠላሳ አምስት ጳጳሳት ይዞ በነሐሴ ወር 449 ዓ.ም. ስብሰባውን ጀመረ፡፡ ጉባኤው የተደረገው እንደበፊቱ በኤፌሶን በቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ነበር፡፡ ጉባኤውም እንደተጀመረ አውጣኪ ተጠርቶ ስለተከሰሰበት ጉዳይ መልስ እንዲሰጥ ተጠየቀ፡፡ አውጣኪ በቊስጥንጥንያ ሕዝብ እጅግ የተወደደና የተደነቀ ከመሆኑም በላይ በቃላት የሚጫወት ቅንነት የጐደለው ሰው ነበር፡፡ አውጣኪ በጉባኤው ፊት ቀርቦ በራሱ እጅ የተጻፈና የፈረመበት የእምነት መግለጫ አቀረበ፡፡ መግለጫውም ከመነበቡ በፊት ራሱ እንዲህ ሲል ጮኾ ተናገረ፡- ‹‹ከልጅነቴ ጀምሮ በግልጥ በምነና (በብሕትውና) ለመኖር ነበር የምፈልገው፡፡ ዛሬ በሕዝብ መካከል በመገኘቴ ታላቅ ሐዘን ይሰማኛል፡፡ ሆኖም እምነቴን ለመመስከር ስለሆነ ደስታ ይሰማኛል፡፡ በኒቅያ ጉባኤ የተወሰነውንና አባታችን የእስክንድርያው ፓትርያርክ ቅዱስ ቄርሎስ ያስተማረውን እምነት በትክክል እቀበላለሁ፤›› አለ፡፡ ከዚህ በኋላ የጉባኤው ጸሓፊ የሚከተለውን የአውጣኪ የእምነት መግለጫ ማንበብ ጀመረ፤ መግለጫውም እንዲህ ይላል፡- ‹‹ሁሉን በያዘ፣ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ አምናለሁ፡፡ በመለኮቱ ከአብ ጋር አንድ በሚሆን በአንድ ልጁ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ፤ ለእኛ ለሰዎች ሲል ለድኅነታችን ከሰማይ ወረደ፡፡ ሥጋ ለበሰ፤ ሰውም ሆነ፡፡ ታመመ፤ ሞተ፤ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ላይ ለመፍረድ ይመጣል፡፡ እርሱ ያልነበረበት ጊዜ ነበረ የሚሉ፣ ከመወለዱም በፊት አልነበረም፤ ካለምንም ተፈጠረ የሚሉት፣ ከአብ ጋር በባሕርዩ የተለየ ነው የሚሉት፣ የእርሱ ሁለቱ ባሕርያት ተቀላቅለዋል ወይም ተዋውጠዋል የሚሉት፣ እነዚህ ሁሉ በአንዲት ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን የተወገዙ ናቸው፡፡ እኔም የምከተለው እምነት ይህ ነው፡፡ በዚህ እምነት እስካሁን ኖሬአለሁ፤ ወደፊትም እስክሞት ድረስ በዚሁ እኖራለሁ፡፡›› የሚል ነበር፡፡ አውጣኪ ይህንን ለጉባኤው ሲያስረዳ ተከትለዉት የመጡትም መነኰሳት አውጣኪ ያቀረበውና የተናገረው ትክክል መሆኑን ከዚያው በጉባኤው ፊት አረጋገጡ፡፡ ስለዚህ ይህን የሃይማኖት መግለጫ ከአዩና ከሰሙ በኋላ አራት ሊቃነ ጳጳሳት ማለት የኢየሩሳሌሙ፣ የአንጾኪያው፣ የኤፌሶኑና የቂሣርው ዘቀጰዶቅያ አውጣኪ በእምነቱ ኦርቶዶክስ ነው በማለት ለጉባኤው አጽንተው ሲናገሩ ሁሉም አውጣኪ ከተከሰሰበት ኑፋቄ ንጹሕ መሆኑን በአንድ ድምፅ ወሰኑ፡፡ ከተላለፈበትም ውግዘት ፈቱት፡፡ ሥልጣነ ክህነቱንም መልሰውለት ወደ ቀድሞው የሓላፊነት ሥራው እንዲመለስ ውሳኔ አስተላለፉ፡፡ የሁለት ባሕርይን ሐሳብ ይቀበል የነበረው የዶሪሊያም ጳጳስ አውሳብዮስ አውጣኪን በመወንጀል መግለጫ ሲያቀርብ በዚያ የተሰበሰቡት መነኰሳትና ምእመናን በታላቅ ድምፅ ‹‹አውሳብዮስ ይቃጠል! አውሳብዮስ በሕይወቱ ይውደም! ክርስቶስን ለሁለት እንደ ከፈለ እሱም ለሁለት ይከፈል!›› እያሉ ይጮኹ ጀመር፡፡ የቊስጥንጥንያን ፓትርያርክ ፍላብያኖስንና አውጣኪን ያወገዙትን ጳጳሳት የሮሙን ፖፕ ልዮን 1ኛን ጭምር አውጣኪን ያለ አግባብ በማውገዛቸውና ሥልጣናቸውን ያለ አግባብ በመጠቀማቸው ጉባኤው ካወገዛቸው በኋላ፣ የሚከተለውን አጭር መግለጫ አወጣ፡- ‹‹ከኒቅያ እስከ ኤፌሶን አባቶቻችን በጉባኤ ተሰብስበው ከወሰኑት ሃይማኖት ሌላ የሚጨምር፣ የሚቀንስ ወይም የሚያሻሽል ቢኖር የተወገዘ ይሁን፡፡›› ዘግይተው የደረሱት የፖፑ መልእከተኞች ዩልዮስና ሬናቱስ የተባሉት ጳጳሳትና ዲያቆን ሂላሩስ ከፖፑ የተላከውን የሃይማኖት መግለጫ ደብዳቤ እንዲነበብ ጠይቀው ነበር፡፡ ነገር ግን ደብዳቤው ‹‹ክርስቶስ ሁለት ባሕርያት አንድ አካል አለው›› ስለሚልና ይህም ከንስጥሮስ ኑፋቄ ጋር ስለሚመሳሰል ጉባኤው እንዲነበብ አልፈቀደም፡፡ በዚህም ምክንያት የፖፑ መልእከተኞች ተቀይመው ወዲያውኑ በድብቅ ከጉባኤው ወጥተው ወደመጡበት ተመለሱ፡፡ የጉባኤውም ውሳኔ በንጉሠ ነገሥቱ በዳግማዊ ቴዎዶስዮስ ጸደቀ፡፡ የቊስጥንጥንያ ፓትርያርክ ፍላብያኖስ በኤፌሶን 2ኛ ጉባኤ እንደተወገዘ ወዲያውኑ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ የዚህን ጉባኤ ውሳኔ ሲሰማ የሮሙ ፖፕ ልዮን ቀዳማዊ እጅግ ተናዶ ጉባኤውን ‹‹ጉባኤ ፈያት (የወንበዴዎች ጉባኤ)›› ብሎ ጠራው፡፡ የጉባኤውንም ሊቀ መንበር ቅዱስ ዲዮስቆሮስን አወገዘው፡፡ ከእስክንድርያ ጋር የነበረውንም ግንኙነት ጨርሶ አቋረጠ፡፡ ፖፑ ይህን ሁሉ ያደረገው እሱ የላከው የሃይማኖት ነክ ደብዳቤ በጉባኤው ላይ ስላልተነበበና የእርሱም መልእክተኞች በጉባኤው ላይ በሙሉ ባለመካፈላቸው ነበር፡፡ በተጨማሪም ፖፑ ለንጉሠ ነገሥቱ ለዳግማዊ ቴዎዶስዮስ የኤፌሶኑን ጉባኤ የዲዮስቆሮስ ጉባኤ ብሎ በመጥራት በጉባኤው ላይ ያለውን ቅሬታ ከገለጸ በኋላ፣ ሌላ ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ (ጉባኤ) እንዲጠራ ጥብቅ ሐሳብ አቀረበ፡፡ እንዲረዳውም የምዕራቡን ክፍል ገዥ (ንጉሥ) የነበረውን ሣልሳዊ ዋሌንቲኒያኖስን () እና ሚስቱን ንግሥት አውዶቅሲያን አጥብቆ ለምኖ ነበር፡፡ እነዚህም ባለሥልጣኖች እያንዳንዳቸው ሐሳቡን በመደገፍ ለንጉሠ ነገሥቱ ለዳግማዊ ቴዎዶስዮስ ደብዳቤ ጽፈው ነበር፡፡ ዳግማዊ ቴዎዶስዮስ ግን ሁለተኛው የኤፌሶን ጉባኤ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያላቸው የቅዱሳን አባቶች ጉባኤ መሆኑን ገልጦ በመጻፍ ስለ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ምንም የሚያሳስብ ነገር አለመኖሩን ገልጦ አሳስቧቸዋል፡፡ በተጨማሪም የምዕራቡን ንጉሥና ንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ መክሯቸው ነበር፡፡ ፖፕ ልዮን ግን ሌላ ዓለም-አቀፍ ሲኖዶስ እንዲደረግ ዳግማዊ ቴዎዶስዮስን አጥብቆ መጠየቁን ቀጠለ፡፡ ሆኖም የፖፑ ጥረት ሁሉ ውጤት አላስገኘም፡፡ ምክንያቱም ዳግማዊ ቴዎዶስዮስ ለ2ኛው የኤፌሶን ጉባኤ ታላቅ አክብሮት ስለነበረውና ውሳኔውንም በሚገባ ስላጸደቀው ነበር፡፡ የኬልቄዶን ጉባኤ ሁለተኛው የኤፌሶን ጉባኤ ከአለፈ ከአንድ ዓመት በኋላ በሐምሌ ወር 450 ዓ.ም. ዳግማዊ ቴዎዶስዮስ በድንገት ከፈረስ ላይ ወድቆ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ ቴዎዶስዮስ ወራሽ ስላልነበረው ለአልጋው ቅርብ የነበረች ታላቅ እኅቱ ብርክልያ () ነበረች፡፡ ብርክልያ ግን በድንግልና መንኵሳ ነበር የምትኖረው፡፡ ሆኖም ብርክልያ ለሥልጣን ስለጓጓች ምንኵስናዋን አፍርሳ የሮም መንግሥት የጦር አዛዥ ጄኔራል የነበረውን መርቅያን () አግብታ በነሐሴ ወር 450 ዓ.ም. እሱ ንጉሠ ነገሥት እሷ ንግሥት ሆነው የሮምን ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ማስተዳደር ጀመሩ፡፡ ይህ የብርክልያ ምንኵስናን ማፍረስ በኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ በተለይም በግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ተቀባይነትን አላገኘም ነበር፡፡ የሮሙ ፖፕ ግን ከአዲሶቹ የሮም መንግሥት ንግሥትና ንጉሠ ነገሥት ዘንድ ተወዳጅነትን ለማግኘት ሲል ጋብቻቸውን በማወደስ አጸደቀላቸው፤ ቡራኬውንም ላከላቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ፖፕ ልዮን ከቊስጥንጥንያ ንጉሣዊ ቤተሰብ ጋር ወዳጅነትን መሠረተ፡፡ እንኳን ደስ አላችሁ ብሎም በጻፈው ደብዳቤ መጨረሻ ላይ እሱ የፈለገው ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ እንዲሰበሰብ አሳሰበ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በንጉሠ ነገሥቱ በመርቅያንና በፖፕ ልዮን መካከል ብዙ የወዳጅነት ደብዳቤዎች ተጻጽፈዋል፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ መርቅያን በሥልጣኑ በ2ኛው በኤፌሶን ጉባኤ የተወገዘው የፍላብያኖስ አስከሬን ፈልሶ በቊስጥንጥንያ በሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ክብር እንዲቀበር አደረገ፡፡ የተጋዙት ጳጳሳትም ከግዞት ወጥተው ወደየሥራቸው እንዲመለሱ አደረገ፡፡ በመሠረቱ በሲኖዶስ የተወገዙት ወደ ቀድሞ ሥራቸው መመለስ የሚችሉት በንጉሥ ትእዛዝ ሳይሆን በጳጳሳት ሲኖዶስ መሆን ስለነበረበት ንጉሡ ያደረገው ሕገ-ወጥ ሥራ ነበር:: ፖፑም የሱ ፍላጎት ስለነበረ ይህንን አልተቃወመም፡፡ በተቃራኒው ንጉሡ የተወገዙት ጳጳሳት ወደየሀገረ ስብከታቸው እንዲመለሱ የፍላብያኖስም አስከሬን ወደ ቊስጥንጥንያ ፈልሶ በክብር እንዲቀበር በማድረጉ ፖፕ ልዮን ለንጉሠ ነገሥቱ ልባዊ ምስጋና አቅርቧል፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ መርቅ ያንና ንግሥቲቱ ብርክልያ 2ኛው የኤፌሶን ሲኖዶስ ባቀረበው የሃይማኖት መግለጫ መሠረት ነፃ ያደረገውን አውጣኪንም ያለ ሲኖዶስ ውሳኔ ወደ ሰሜን ሶርያ እንዲጋዝ አደረጉ፡፡ ፖፕ ልዮን በአሳሰበው መሠረት ንጉሥ መርቅያን ጥቅምት 8 ቀን 451 ዓ.ም. ዓለም-አቀፍ ሲኖዶስ እንዲደረግ ለጳጳሳት ሁሉ ጥሪ አስተላለፈ፡፡ ጉባኤውም እንዲደረግ የታሰበው ከቊስጥንጥንያ 96 ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኝ በኒቅያ ነበር፡፡ ነገር ግን በጸጥታ ምክንያት ከቊስጥንጥንያ 3 ኪሎ ሜትር ብቻ ርቃ በምትገኘው በኬልቄዶን እንዲሆን ንጉሡ ስለ ወሰነ ጉባኤው በኬልቄዶን ሆነ፡፡ ንጉሥ መርቅያንና ንግሥት ብርክልያ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ተገኝተዋል፡፡ ጉባኤው በሥነ ሥርዓት መካሄዱን የሚቆጣጠሩ 18 ዳኞች በንጉሡ ተሠይመው ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ ዳኞች መሠየማቸው መንግሥት ሲኖዶሱን ምን ያህል እንደተቈጣጠረው ያመለክታል፡፡ የጉባኤው አባላት አቀማመጥ እንደሚከተለው ነበር፤ ዳኞቹ በመኻል ከዳኞቹ በስተግራ የፖፑ መልእክተኞች፣ ቀጥሎ የቊስጥንጥንያው አናቶልያስ፣ የአንጾኪያው ማክሲሙስ፣ የቂሣርያውና የኤፌሶኑ ጳጳሳትና ሌሎች የምሥራቅና የመካከለኛው ምሥራቅ አህጉር ጳጳሳት ሲሆኑ፣ በቀኝ በኩል ቅዱስ ዲዮስቆሮስ፣ የኢየሩሳሌም፣ የተሰሎንቄ፣ የቆሮንቶስ፣ የግብጽ፣ የኢሊሪኩም፣ የፍልስጥኤም ጳጳሳትና ሌሎች ጳጳሳት ተቀምጠዋል፡፡ በኤፌሶን ጉባኤ የተወገ ዙትን ንስጥሮሳውያን መናፍቃንን የቂሮስ ኤጲስቆጶስ ቴዎዶሪጦስንና የኤዴሳን ኤጲስቆጶስ ኢባንን የዚህ ጉባኤ አባላት አድርገው ተቀበሏቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ብዙ ብጥብጥ ተነሣ፤ የግብጽ ጳጳሳት በኤፌሶን ጉባኤ የተወገዙትን ንስጥሮሳውያን ቴዎዶሪጦስንና ኢባንን ጉባኤው በአባልነት በመቀበሉ ‹‹አይሁዶችን፣ የክርስቶስን ጠላቶች ከዚህ አስወጡ!›› እያሉ በመጮኽ ተቃውሟቸውን አሰሙ፡፡ ጉባኤው ግን የእነሱን ጩኸት ከቁም ነገር አልቈጠረውም፡፡ ጉባኤውን በሊቀ መንበርነት በተራ የመሩት ከመንግሥት የተሠየሙት ዳኞችና የሮሙ ፖፕ መልእከተኞች ነበሩ፡፡ የሮሙ ተወካዮች ጉባኤውን ሲመሩ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ ነበር፡፡ ከአሁኑ በስተቀር ባለፉት ዓለም-አቀፍ ሲኖዶሶች ሁሉ የእስክንድርያው ፓትርያርክ ከሊቃነ መናብርቱ ዋናው ነበር፡፡ አሁን ግን የእስክን ድርያውን ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስን ለመኰነን የተሰበሰበ ሲኖዶስ ስለሆነ ዲዮስቆሮስ ከሊቃነ መናብርቱ አንዱ አልሆነም፡፡ የጉባኤው አባላት ቦታቸውን ይዘው እንደተቀመጡ የሮሙ ፖፕ ተወካይ ፓስካሲኑስ () ተነሥቶ ለዳኞቹ ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ከተቀመጠበት ቦታ ማለት ከጉባኤው እንዲነሣና ሌላ ቦታ እንዲቀመጥ አመለከተ፡፡ የመንግሥቱ ዳኞች ለምን ይነሣል ብለው በጠየቁ ጊዜ፣ ሌላው የፖፑ መልእክተኛ ሊሴንቲያስ () የተባለው ዲዮስቆሮስ ከዚህ በፊት የሮሙ ፖፕ ሳይፈቅድ በሥልጣኑ ሲኖዶስ (የ449 ሲኖዶስን ማለቱ ነው) እንዲካሄድ አድርጓል በማለት ክስ አቀረበ፡፡ ይህ ግን መሠረት የሌለው ክስ ነበር፡፡ ምክንያቱም ከዚህ በፊት የተደረጉት ሲኖዶሶች ሁሉ የተጠሩትና የተካሄዱት በሮም ንጉሠ ነገሥት ፈቃድና ትእዛዝ እንጂ በሮሙ ፖፕ ፈቃድ አልነበረም፡፡ ያለፈውም የሁለተኛው የኤፌሶን ሲኖዶስ የተጠራው በዳግማዊ ቴዎዶስዮስ ትእዛዝ እንጂ በፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ሥልጣን አልነበረም፡፡ ስለዚህ የቀረበው ክስ ዳኞቹን አላረካ ቸውም፡፡ በዚህ ጉዳይ ብዙ ጭቅጭቅ ስለተፈጠረ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ በፈቃዱ ቦታውን ለቆ ተከሳሾች በሚቀመጡበት ቦታ ሄዶ ተቀመጠ፡፡ የሮሙ ፖፕ ተወካዮች በሁለተኛው የኤፌሶን ጉባኤ ፓትር ያርክ ዲዮስቆሮስ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና አፍርሷል ሲሉ ከሰሱ፡፡ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ሲመልስ እሱ በንጉሠ ነገሥቱ በቴዎ ዶስዮስ ትእዛዝና ጥያቄ መሠረት ነው ጉባኤውን የመራው፡፡ እሱ ቀኖናን አፈረሰ? ወይስ በኤፌሶን ጉባኤ የተወገዙትን ንስጥሮሳውያን መናፍቃንን የቂሮስ ኤጲስ ቆጶስ ቴዎዶሪጦስንና የኤዴሳን ኤጲስቆጶስ ኢባንን የዚህ ጉባኤ አባላት አድርገው የተቀበሉት እነሱ ናቸው ቀኖና አፍራሾች? ብሎ ጥያቄ አቀረበ፡፡ ሆኖም ይህ የፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ጥያቄ ምንም መልስ ሳይሰጠው በዝምታ ታለፈ፡፡ ቀጥሎ በ2ኛው የኤፌሶን ጉባኤ የተወገዘው የዶሪሌኡም ኤጲስቀጶስ አውሳብዮስ ተነሥቶ ዲዮስቆሮስ እሱንና የቊስጥንጥንያውን ፍላብያኖስን ‹‹ምንም የሃይማኖት ጕድለት ሳይገኝብን ያለ አግባብ አውግዞናል ጥቃትም አድርሶብናል፡፡ በተጨማሪም አውጣኪን ከግዝቱ በመፍታት የኦርቶዶክስ እምነትን አበላሽቷል፤›› በማለት ክስ አቀረበ፡፡ ይህ ተመሳሳይ ክስ በሮሙ ፖፕ ተወካዮችም ቀርቧል፡፡ በመሠረቱ ይህ ክስ እውነት እንኳ ቢሆን የሚመለከተው ሲኖዶሱን እንጂ የሲኖዶሱን ሊቀ መንበር ዲዮስቆሮስን አልነበረም፡፡ ከዚህ ላይ ልንገነዘበው የሚገባው የሮሙ ፖፕ ተወካዮችም ሆኑ ከሳሹ አውሳብዮስ በአጠቃላይ የኬልቄዶን ጉባኤም ቢሆን ዲዮስቆሮስን በእምነት ክህደት አልከሰሱትም፡፡ ሆኖም መናፍቅ ነው ተብሎ የታሰበውን አውጣኪን የ449 ዓ.ም. ሲኖዶስ ነጻ አድርጎ ከውግዘቱ ስለፈታው ብቻ ዲዮስቆሮስን የአውጣኪን የኑፋቄ ትምህርት ተቀብሏል ብለው በጭፍኑ ደምድመዋል፡፡ አውጣኪ ግን በፊት ያስተምር የነበረውን የኑፋቄ ትምህርት ትቶ በቃልም በጽሑፍም ኦርቶዶክሳዊ የእምነት መግለጫ በማቅረቡ በዚህ መሠረት ነው 2ኛው የኤፌሶን (የ449) ሲኖዶስ ነጻ ያደረገው፡፡ ስለዚህ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ አውጣኪ ያቀረበው የእምነት መግለጫ የሚገኝበት የ449 ሲኖዶስ ቃለ ጉባኤ እንዲነበብ ጠየቀ፡፡ የ449 ሲኖዶስ ቃለ ጉባኤ የመጀመሪያው ክፍል ከተነበበ በኋላ ጉባኤውን የጠራው ንጉሡ ዳግማዊ ቴዎዶስዮስ መሆኑና አውጣኪንም ነጻ ያደረጉት በጉባኤው የነበሩት ጳጳሳት በሙሉ ተስማምተው በፊርማቸው ያጸደቁት መሆኑ ተነበበ፡፡ በ449 ዓ.ም. በ2ኛው የኤፌሶን ሲኖዶስ ላይ የነበሩት ጳጳሳት ግን የ449 ሲኖዶስን ውሳኔ ፈጽሞ እንደማያውቁት የፈረሙትም በወታደሮች ተገደው በባዶ ወረቀት ላይ መሆኑን አጥብቀው ተናገሩ:: የግብጽ ጳጳሳት ግን ይህን በሰሙ ጊዜ ‹‹የክርስቶስ ወታደር የዚህን ዓለም ባለሥልጣን ፈጽሞ አይፈራም፡፡ እሳት አንድዱ አንድ ሰማዕት እንዴት እንደሚሞት እናሳያችሁ!›› ብለው በጉባኤው ፊት ተናገሩ፡፡ ባዶ ወረቀት ላይ ነው የፈረምነው ካሉት አንዱ የኤፌሶኑ ኤጲስ ቆጶስ እስጢፋኖስ ነበር፡፡ ይህ ሰው አውጣኪ ነጻ እንዲደረግ ተነሥተው ከተናገሩት ሰዎች ሁለተኛው ነበር፡፡ አውሳብዮስና ፍላብያኖስም እንዲወገዙ ከተናገሩት 5ኛው ተናጋሪ እሱ ነበር፡፡ የሲኖዶሱ ጸሓፊ በ449 ሲኖዶስ ቃለ ጉባኤ ላይ የአውጣኪን የሃይማኖት መግለጫ ሲያነብ አንዳንድ አባቶች ይህን መግለጫ እንዳላዩትና ፊርማቸውም አስመስሎ የተፈረመ ነው በማለት ካዱ፡፡ ከዚህ በኋላ በጉባኤው ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ እምነቱን እንዲገልጽ ተጠይቆ ሁለቱ ባሕርያት (የመለኮትና የሥጋ) ያለ መቀላቀልና ያለ ትድምርት፣ ያለ መለወጥና ያለ መለያየት በአንድ አካል እንደተዋሐዱ በሚገባ አስረዳ፡፡ እንዲሁም በቅዱስ ቄርሎስ ትምህርት መሠረት ‹‹አአምን በአሐዱ ባሕርይ (ህላዌ) ዘቃለ እግዚአብሔር ሥግው፤›› ብሎ አስረዳ፡፡ ጉባኤውም በዚህ በዲዮስቆሮስ እምነት ላይ ምንም እንከን፣ ምንም ስሕተት አላገኘም፡፡ ጉባኤው በሌላ መንገድ ‹‹አውጣኪ በጽሑፍ ካቀረበው የተለየ በቃል ቢናገር ምን ትፈርድ ነበር?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ፣ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ‹‹አውጣኪ የጻፈውን ትቶ ሌላ የክህደት ነገር ቢናገር፣ እሱን ማውገዝ ብቻ ሳይሆን በእሳትም እንዲቃጠል እፈርድበት ነበር፤›› ብሎ መለሰ፡፡ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ በእንደዚህ ያለ ነጐድጓዳዊ አነጋገር ሁሉን ግልጥልጥ አድርጎ በተናገረ ጊዜ፣ ኬልቄዶናውያን ጸጥ አሉ፡፡ ዲዮስቆሮስን በመቃወም የተናገሩ የምሥራቅ አህጉር ጳጳሳት ግን ንግግሩ ልባቸውን ነክቶት ‹‹በድለናል፤ ይቅርታ እንጠይቃለን!›› በማለት ጮኹ፡፡ የመንግሥቱ ዳኞች በባዶ ወረቀት ላይ ነው የፈረምነው ስላሉት እንደገና ሲጠይቋቸው ‹‹በድለናል፤ ይቅርታ እንጠይቃለን፤›› ሲሉ መለሱ፡፡ እንደገና ፍላብያኖስን ዲዮስቆሮስ ነው ያስገደለው ስላሉት ቢጠየቁ አሁንም ‹‹በድለናል፤ ይቅርታ እንጠይቃለን፤›› ሲሉ መለሱ፡፡ በዚህ ሁኔታ እነዚህ ጳጳሳት 1ኛ/ በሐሰት በባዶ ወረቀት ላይ ፈርመናል በማለታቸውና፣ 2ኛ/ ፍላብያኖስንና አውሳብዮስን ያለ አግባብ በማውገዛቸው ይቅርታ ጠየቁ፡፡ የመንግሥቱ ዳኞች ፍላብያኖስ ኦርቶዶክስ መሆኑን አጥብቀው በጠየቁ ጊዜ፣ የሮሙ ተወካዮችና አብዛኞቹ አባላት በ449 ሲኖዶስ ጊዜ የነበሩትም ጭምር ፍላብያኖስ ኦርቶዶክስ እንደነበረ ተናገሩ፤ ‹‹ታዲያ ለምን ተወገዘ?›› ሲሉ ዳኞቹ ጠየቁ፡፡ በዚህ ጊዜ ዲዮስቆሮስ ፍላብያኖስ ‹‹ክርስቶስ ከሥጋዌ በኋላ ሁለት ባሕርያት እንዳለው አጥብቆ ይናገር ነበር፤›› ብሎ ተናገረ፡፡ የዚህም እውነት እንዲወጣ ብሎ የ449 ሲኖዶስ ቃለ ጉባኤ ቀርቦ እንዲነበብ አበክሮ ጠየቀ፡፡ ለዚህ ምንም መልስ አልተሰጠውም፡፡ ሁሉም ዳኞቹም ጭምር ቃለ ጉባኤው እንዳይነበብ ስለፈለጉ ጸጥ አሉ፡፡ ሁሉም ዝም ቢሉም ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ንግግሩን በመቀጠል ፍላብያኖስ ‹‹ክርስቶስ ከሥጋዌ በኋላ ሁለት ባሕርያት አለው፤›› እያለ እንደሚናገር መልሶ መላልሶ አስረዳ፡፡ የቀድሞ አባቶች ግን ለምሳሌ አትናቴዎስ፣ ጎርጎርዮስና ቄርሎስ ‹‹አሐዱ ባሕርይ ዘእግዚአብሔር ቃል ሥግው›› እንጂ ከተዋሕዶ በኋላ ‹‹ሁለት ባሕርያት›› ፈጽሞ እንደማይሉ በመጻሕፍቶቻቸው ሁሉ ለማንበብ እንደሚቻል አስረዳ፡፡ የቀረቡትን ማስረጃዎች ሁሉ ከቁም ነገር ሳያስገቡ ጉባኤውም በሚገባ ሳይወያይበት ዳኞቹ በጭፍን ፍላብያኖስና አውሳብዮስ ያላግባብ ነው የተወገዙት በማለት ውሳኔ አሳለፉ፡፡ በተጨማሪም አውጣኪ ቀርቦ ሳይጠየቅ ለ449 ጉባኤ ያቀረበውንም የሃይማኖት መግለጫ ሳይመለከቱ፣ በጭፍን በ449 ሲኖዶስ ላይ ያለ አግባብ ነው ነጻ ሆኖ ከግዝቱ የተፈታው ብለው ዳኞቹ፣ የፖፑ ተወካዮችና ሌሎቹ የጉባኤው አባላት ወሰኑ፡፡ ይህ በግልጥ የሚያመለክተው የኬልቄዶን ጉባኤ የተጠራው ዲዮስቆሮስንና አውጣኪን ለማውገዝና ፍላብያኖስንና አውሳብዮስን ነጻ ለማድረግ መሆኑን ነው፡፡ ከላይ ለቀረቡት ጥብቅ ማስረጃዎች ምንም መልስ ሳይሰጡ የመንግሥቱ ዳኞችና የሮሙ ፖፕ እንደራሴዎች የፖፑን የዶግማ ደብዳቤ () አስተያየቱን እንዲገልጥ ለፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ሰጡት፡፡ ዲዮስቆሮስም ለጥቂት ጊዜ ከአነበበው በኋላ፣ ደብዳቤው ኦርቶዶክሳዊ ሳይሆን ንስጥሮሳዊ መሆኑን ገልጦ ደብዳቤውንና ደራሲውን ያለ አንዳች ማመንታት አወገዘ፡፡ ከተሰበሰቡት ጳጳሳት ብዙዎቹ ስለ ልዮን ደብዳቤ () የዲዮስቆሮስን አስተያየትና ስሜት ተጋርተዋል፡፡ ነገር ግን አስተያታቸውን በይፋ ለመግለጥ ድፍረት አልነበራቸውም፡፡ ሌሎች ደግሞ ስለዚሁ ደብዳቤ ታላቅ ጥርጣሬና መደናበር እንዳደረባቸው በፊታቸው ላይ ይነበብ ነበር፡፡ ይህን የአባላቱን ሁኔታ የተመለ ከቱት ዳኞች በደብዳቤው ውስጥ የሚያውክና የሚያስቸግር ነገር እንዳለ ጥያቄ አቀረቡ፡፡ አንዳንድ ጳጳሳት ምንም ችግር አለመኖሩን ገልጠው፣ ሆኖም አንዳንድ የላቲን ቃላትንና አባባሎችን በደንብ ለመመርመር ጊዜ ለማግኘት ስብሰባው ለአምስት ቀናት እንዲበተን ጠየቁ፡፡ ጥያቄአቸውም ወዲያውኑ ተቀባይነት አግኝቶ ስብሰባው ተበተነ፡፡ ነገር ግን ከሦስት ቀናት በኋላ ጳጳሳቱ የመንግሥቱ ዳኞች በሌሉበት ለነሱም ሳይነግሩ ይፋዊ ስብሰባቸውን በፖፑ እንደራሴ ፓስካሲኑስ () ሊቀ መንበርነት ቀጠሉ፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ የግብጽ ጳጳሳትና ሌሎች ብዙ ጳጳሳት አልተገኙም፡፡ ስብሰባውን እንደጀመሩ የፖፑ እንደራሴና የስብሰባው ሊቀ መንበር ‹‹የፖፑ ደብዳቤ መከበር አለበት፡፡ ሁሉም ደብዳቤውን መቀበል አለባቸው፡፡ ይህን ደብዳቤ የሚቃወም ተከሶ በጉባኤው ፊት መቅረብ አለበት፤›› ሲል አወጀ፡፡ ወዲያውኑ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወደ ስብሰባው እንዲመጣ ወደ ማረፊያ ቦታው ሦስት ጳጳሳትና አንድ ዲያቆን ተላኩ፡፡ በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከቤት እንዳይወጣ ንግሥት ብርክልያ ባዘዘቻቸው ወታደሮች ይጠበቅ ነበር፡፡ መልእክተኞቹም ዲዮስቆሮስን ወደ ጉባኤው እንዲመጣ በጠየቁት ጊዜ፣ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ‹‹ጉባኤው የተበተነው ለአምስት ቀናት ሲሆን አሁን ገና ሦስት ቀናት ነው ያለፉት፡፡ አሁን እንዴት ለመሰብሰብ እንችላለን? ለመሆኑ የመንግሥቱ ተወካዮች ዳኞች ተነግሯቸዋል?›› ብሎ ጠየቀ፡፡ ለመጀመሪያው ጥያቄ መልስ አልተሰጠውም፡፡ ለሁለተኛው ጥያቄ ግን ‹‹ለቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ምእመናን አያስፈልጉም፤›› ሲሉ መለሱለት፡፡ ቀጥሎ ከቤት ወጥቶ ወደ ስብሰባው ለመሄድ ይፈቅዱለት እንደሆነ ወታደሮቹን ማስፈቀዳቸውን መልእክተኞቹን ጠየቀ፡፡ እነርሱም በበኩላቸው ‹‹እኛ የተላክነው አንተን እንድንጠራ ነው እንጂ ወታደሮችን እንድንጠይቅ እይደለም፤›› ሲሉ መለሱና ተመልሰው ሄዱ፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ሌሎች መልእክተኞች ለዲዮስቆሮስ ሌላ ጥሪ አቀረቡ፡፡ እሱም የመንግሥት ተወካዮች ዳኞች ከሌሉ እንደማይ መጣ ነግሯቸው ተመለሱ፡፡ ይህ ሁሉ የተደረገው በሲኖዶስ ሕግ መሠረት አንድ ሰው ሦስት ጊዜ ተጠርቶ ካልመጣ እንደሚወገዝ ስለሚያውቁ በዚሁ መሠረት ዲዮስቆሮስን በሌለበት ለማውገዝና የፖፕ ልዮንን የዶግማ ደብዳቤ () ሁሉም እንዲቀበሉት ለማድረግ ነበር፡፡ ይህም የታቀደው በፖፑ ወኪሎች ነበር፡፡ በዚህ መካከል ሌሎች ከሳሾች ቀርበው በፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ላይ የተለያዩ እምነትን የማይመለከቱ የሐሰት ክሶችን እንዲያቀርቡ ተደረገ፡፡ በመጨረሻም ዲዮስቆሮስ ወደ ጉባኤው እንዲመጣ ለሦስተኛ ጊዜ መልእክተኞች ላኩበት፡፡ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ የኬልቄዶን ጉባኤ ሤራ በደንብ ስለገባው የሃይማኖት መልእክቱን ቀደም አድርጎ ያስተላለፈ መሆኑን ገልጾ በሕመም ምክንያት ወደ ጉባኤው ለመሄድ አለመቻሉን ስለገለጠላቸው መልእክተኞቹ ተመልሰው ሄዱ፡፡ የፖፑ ተወካዮችና አንዳንድ የእነርሱ ደጋፊዎች ዲዮስቆሮስን ለማውገዝ ይህንኑ ነበር የፈለጉት፡፡ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ በኬልቄዶናውያን መወገዝ የሮሙ ፖፕ ልዮን፣ የሮም የምሥራቁ ክፍል ንጉሠ ነገሥት የመርቅያንና የንግሥቲቱ የብርክልያ ታላቅ ተጽእኖ የነበረበት ይህ የኬልቄዶን ጉባኤ መጀመ ሪያም የተሰበሰበው ዲዮስቆሮስን ለማው ገዝና ከሥልጣኑ ለማውረድ ስለነበረ፣ እሱን ለማውገዝ ብዙ ምክንያቶች ይፈልጉ ነበር፡፡ በሃይማኖት በኩል ምንም ስሕተት ስላላገኙበት የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና አፍርሷል በማለት እሱን ወንጀለኛ ለማድረግ አስበው ሕጉን የሚያስከብሩት የመንግሥት ዳኞች ለአምስት ቀናት ጉባኤውን በበተኑበት ጊዜ ከግማሽ ያነሱ አባላት ተሰብስበው ቅዱስ ዲዮስቆሮስ በጉባኤው ላይ እንዲገኝ ሦስት ጊዜ ደጋግመው ጥሪ እንዲደርሰው አደረጉ፡፡ ዲዮስቆሮስም ከላይ እንደተገለጸው ሕግ አስከባሪዎቹ ዳኞችና ሌሎች ከእርሱ ጋር የተከሰሱት በሌሉበት ለመገኘት ስላልፈለገ በጉባኤው ላይ አልተገኘም፡፡ ይህን ምክንያት አድርገው ‹ሲያሻኝ ጭስ ወጋኝ› እንደሚሉት ቀኖና አፍርሷል በማለት የተሰበሰቡት በአንድ ድምፅ አወገዙት፡፡ ሲያወግዙትም ሦስት ምክንያቶች ዘርዝረዋል፤ 1ኛ/ በመናፍቅነት የተከሰሰውንና የተወገዘውን አውጣኪን ነጻ አድርጎ ወደ ቤተ ክርስቲያን አንድነት መልሶታል፡፡ ከዚህ ላይ አውጣኪ በጽሑፍ ያቀረ በውንና በቃልም ያረጋገጠውን ኦርቶዶክሳዊ የሃይማኖት መግለጫ ሊመለከ ቱት አልፈለጉም፡፡ 2ኛ/ የሮሙ ፖፕ ልዮን የላከውን የሃይማኖት መግለጫ ደብዳቤ () ባለመ ቀበል ደብዳቤውንም ፖፕ ልዮንንም አውግዟል የሚል ነው፡፡ 3ኛ/ በጉባኤው ላይ እንዲገኝ ሦስት ጊዜ ተጠርቶ አልተገኘም የሚል ነበር፡፡ ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ከተወገዘና ከሥልጣን እንዲወርድ ከተወሰነበት በኋላ ንግሥት ብርክልያ በግል አስጠርታ ሐሳቡን ለውጦ በልዮን ጦማር () ላይ እንዲስማማና እንዲፈርም ትእዛዝ አዘል ምክር ሰጥታው ነበር ይባላል፡፡ እሱ ግን መንፈሰ ጠንካራ ስለነበር የንግሥቲቱን ትእዛዝና ምክር አልተቀበለም፡፡ በዚህ ተናዳ ንግሥቲቱ ቅዱስ ዲዮስቆሮስን በወታደሮች በሚያሰቅቅ ሁኔታ አስደበደበችው፡፡ በዚህም ድብደባ ጥርሶቹ ወላልቀው ጽሕሙም ተነጫጭቶ ነበር፡፡ እሱም የተነጨ ጽሕሙንና የወለቁትን ጥርሶች በአንድ ላይ ቋጥሮ ‹‹ይህ የሃይማኖት ፍሬ ነው፤›› የሚል ጽፎበት ለግብጽ ምእመናን ልኮላቸዋል ይባላል፡፡ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወደ ግዞት መላክ እጅግ የሚገርመው የኬልቄዶን ጉባኤ ስብሰባውን ሳይፈጽም የጉባኤውም ዘገባ ገና ሳይደርሰው የቊስጥ ንጥንያ ንጉሠ ነገሥት መርቅያን የጉባኤውን ውሳኔዎች ሁሉ የሚያጸድቅ ጽሑፍ ለጉባኤው ላከ፡፡ እንዲሁም ንጉሡ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጋግራ (ጋንግራ) ወደሚባል ደሴት እንዲጋዝ ትእዛዝ አስተላለፈ፡፡ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወደተጋዘበት ወደ ደሴተ ጋግራ በሄደ ጊዜ በፈቃዳቸው ሁለት ጳጳሳትና ሁለት ዲያቆናት ተከትለዉት ሄደው ነበር፡፡ ሦስተኛው ጻድቅ የነበረ መቃርዮስ የተባለ የኤድኮ ጳጳስ አብሮት ለመሄድ በመንገድ ላይ ሳለ ‹‹ቅዱስ ማርቆስ ደሙን ባፈሰሰበት ከተማ የሰማዕትነት አክሊል ስለሚጠብቅህ ቶሎ ብለህ ሂድ እንዳያመልጥህ፤›› ብሎ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ስለነገረው ወዲያውኑ ወደ ግብጽ ሄደ፡፡ ንጉሠ ነገሥት መርቅያን ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስን ወደ ግዞት እንዲላክ ከአደረገ በኋላ የጉባኤው ውሳኔ በመንግሥት መጽደ ቁን በመግለጽ ለእስክንድርያና ለመላዋ የግብጽ ሕዝብና ለግብጽ ቤተ ክርስቲያን መልእክት ላከ፡፡ ወዲያውኑም በዲዮስቆሮስ ምትክ ፕሮቴሪዮስ የሚባል ኤጲስ ቆጶስ በቊስጥ ንጥንያ ሹሞ ወደ እስክንድርያ በብዙ ወታደሮች ታጅቦ እንዲሄድ አደረገ፡፡ ወታደሮቹም ለአዲሱ ፓትርያርክ የማይታዘዙትንና የማይገዙትን ከባድ ቅጣት እንዲቀጡ በጥብቅ ታዝዘው ነበር፡፡ የግብጽ ክርስቲያኖች ግን ለዲዮስቆሮስ ታማኝነታቸውን በመግለጥ ንጉሡ ለላከው ፓትርያርክ አንገዛም አሉ፡፡ የግብጽ ጳጳሳትም አስቸኳይ ስብሰባ አድርገው ለፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ታማኝነታቸውን በአንድ ድምፅ ገልጠው፣ ፖፕ ልዮንንና የልዮንን ጦማር () እንዲሁም የኬልቄዶንን ጉባኤን ጉባዔ ከለባት ብለው በመጥራት አወገዙት፡፡ ፓትርያርክ አንዲሆን የተላከባቸውንም ፕሮቴሪዮስን አወገዙ፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ መርቅያንም ይህን እንደሰማ አጸፋውን ለመመለስ ጳጳሳቱ በሙሉ በኬልቄዶን ጉባኤ ውሳኔና በልዮን ጦማር ላይ እንዲ ፈርሙ በግብጽ ለነበሩት የጦር ሹማም ንቱና መኰንኖቹ ትእዛዝ አስተላለፈ፡፡ መኰንኖቹም በትእዛዙ መሠረት ጽሑፎቹን ለማስፈረም ወደየጳጳሳቱ ሲሄዱ መጀመሪያ የተገኘው ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወደ ግዞት ሊከተለው ሲል ‹‹ወደ እስክን ድርያ ሂድ፤ በዚያ የሰማዕትነት አክሊል ይጠብቅሃል፤›› ያለው የኤድኮ ጳጳስ አባ መቃርዮስ ነበር፡፡ ወታደሮቹ ጽሑፎቹን አልፈርምም በማለቱ ከዚያው ደብድበው ገድለውታል፡፡ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነታቸው በመጽናታቸውና የኬልቄዶንን ጉባኤ ባለመቀበላቸው ሠላሳ ሺሕ የሚሆኑ ካህናትና ምእመናን ተገድለዋል፡፡ ከጥቂት የሰበካ አብያተ ክርስቲያናት በስተቀር አብዛኞቹ የአብያተ ክርስቲያናት ሕንጻዎች የኬልቄዶንን ጉባኤ ለሚደግፉ ጥቂት ክርስቲያኖች በንጉሠ ነገሥቱ ትእዛዝ እንዲሰጣቸው ተደረገ፡፡ ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ አምስት ዓመት በግዞት ግፍና ሥቃይ እየተቀበለ ከቆየ በኋላ በ456 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ መላው የግብጽ ካህናትና ምእመናን የአባታቸውን ማረፍ በሰሙ ጊዜ ታላቅ ሐዘን ተሰማቸው፡፡ ወዲያውኑ ካህናቱና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው የዲዮስቆሮስ ዋና ጸሓፊ የነበረውን ጢሞቴዎስ የተባለውን አባት በአንድ ድምፅ መርጠው በዲዮስቆሮስ ፋንታ ዳግማዊ ጢሞቴዎስ ተብሎ የእስክን ድርያ 26ኛው ፓትርያርክ ሆኖ እንዲሾም አደረጉ፡፡ ይህ ምርጫ በሚካሄድበት ጊዜ የንጉሠ ነገሥቱ የመርቅያን ዋና እንደራሴ አገረ ገዥው በእስክንድርያ አልነበረም፡፡ ገዥው ሲመለስ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን አዲስ ፓትርያርክ መርጠው መሾማቸውን በሰማ ጊዜ እጅግ ተናደደ፡፡ አገረገ ዥውም ግብጻውያን ፓትርያርክ የመምረጥ መብት እንዳልነ በራቸው ነገራቸው፡፡ ለማናቸውም እርሱ እስከሚመለስ ድረስ መጠበቅ ነበረባቸው በማለት ምርጫውን እንደማይቀበለው በግልጥ ነገራቸው፡፡ ለእነሱ የተሾመላቸ ውንና መንግሥትም የሚቀበለውን ፕሮቴሪዮስን የግድ መቀበልና ለእርሱ መታዘዝ እንዳለባቸው ነግሮአቸው ሌላ ፓትርያርክ መምረጥ በመንግሥት ላይ እንደማመፅ የሚያስቆጥርና ከባድ ቅጣት የሚያስከትል ነው በማለት አስጠነቀቃቸው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አዲሱ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ዳግማዊ ጢሞቴዎስ ጳጳሳቱን በሙሉ ጠርተው ሲኖዶስ አደረጉና የኬልቄዶንን ጉባኤና የጉባኤውን ደጋፊዎች እንደገና አወገዟ ቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ዲዮኒስዮስ የሚባል አንድ የመንግሥት ወታደራዊ ከፍተኛ ባለሥልጣን ከቊስጥንጥንያ ተልኮ መጣ፡፡ የመጣውም የግብጽ ክርስቲያኖች በሙሉ መንግሥት የሾመውን ፕሮቴሪ ዮስን እንዲቀበሉ ለማድረግ ነበር፡፡ ለእርሱም የማይታዘዙትን ከባድ ቅጣት እንዲቀጣቸው ሥልጣን ተሰጥቶት ነበር የመጣው፡፡ ይህ ባለሥልጣን በመጣ ጊዜ ፓትርያርክ ዳግማዊ ጢሞቴዎስ ከእስክንድርያ ወጥተው የተለያዩ ሀገረ ስብከቶችን በመጐብኘት ላይ ነበሩ፡፡ ፓትርያርኩ በተመለሱ ጊዜ መንበረ ሊቀ ጵጵስናቸው ውጭውም ውስጡም በመንግሥት ቊልፍ ተቈልፎ አገኙት፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑ በዚህ እጅግ ተናደው መንግሥት ወደሾመው ፓትርያርክ ወደ ፕሮቴሪዮስ ሄደው በንጉሡ የተሾመውን ፓትርያርክ ከተደበቀበት አውጥተው ገደሉት፡፡ ይህ ዓመፅ መንግሥትን ስላሳሰበ በሕዝብ ላይ አጸፋዊ እርምጃ ለመውሰድ አልተፈለገም፡፡ ሆኖም ንጉሥ መርቅያን ግብጻውያን የመረጡት ፓትርያርክ ጢሞቴዎስና ወንድሙ ተይዘው ዲዮስቆሮስ ታስሮበት በነበረበት በደሴተ ጋግራ እንዲጋዙ አደረገ፡፡ ይህንም ያደረገው የሕዝቡን መንፈስ ለመስበርና ተስፋ ለማስቈረጥ ነበር፡፡ የሕዝቡ መንፈስ ግን ፈጽሞ አልተለወጠም፡፡ የቊስጥንጥንያ መንግሥት ደጋግሞ ፓትርያርክ ቢልክም ግብጻውያን ግን መንግሥት የሚልካቸውን ፈጽሞ አይቀበሉም ነበር፡፡ እስከ ኬልቄዶን ጉባኤ ድረስ በግብጽ የነበሩ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በቅዳሴና በሌሎች የጸሎት አገልግሎት ጊዜ በግሪክኛ ቋንቋ ነበር የሚጠቀሙት፡፡ ከዚህ በኋላ ግን በቅብጥ ቋንቋ መጠቀም ጀመሩ፡፡ ከ451 ዓ.ም. ጀምሮ ማለት ከኬልቄዶን ጉባዔ በኋላ አንዲት ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ተከፈለች፡፡ በአንድ በኩል የሮም ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ሙሉ ድጋፍ የነበራቸው እኛ መለካውያን ብለን የምንጠራቸው የምዕራቡ አብያተ ክርስቲያናት የሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንና የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች የሆኑ ሁሉ ሲሆኑ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የምሥራቅ ወይም የኦርየንታል ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ማለት የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የሶርያ፣ የአርመንና የሕንድ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው፡፡ የፖፕ ልዮን ቀዳማዊ የሃይማኖት መግለጫ ጦማር የልዮን የሃይማኖት መግለጫ ጦማር (ደብዳቤ) () የሚከተሉት ነጥቦች ነበሩት፡- 1ኛ/በክርስቶስ ውስጥ የመለኮት ባሕርይና የትስብእት ባሕርይ በአንድ አካል አንድ ሆኑ፤ ያለ መቀላቀል፣ ያለ መለያየትና ያለ መለወጥ፡፡ 2ኛ/ እያንዳንዱ ባሕርይ የግብር ክልሉን ጠብቆ ይኖራል፡፡ ይህም ማለት መለኮት የመለኮትን ሥራ ይሠራል፤ ትስብእትም የትስብእትን ሥራ ይሠራል፡፡ 3ኛ/ ‹‹ከመዋሐድ በፊት ሁለት ነበሩ፤ ከተዋሐዱ በኋላ ግን አንድ ባሕርይ ነው ማለት ሞኝነት ነው፤›› የሚል ኃይለ ቃል ይገኝበታል፡፡ ከልዮን ጦማር ውስጥ ከዚህ በላይ የገለጥናቸው አንድ አካል ከማለቱ በስተቀር የንስጥሮስን ትምህርት ነው የሚገልጡት፡፡ ሁለቱ ባሕርያት አንድ ሆኑ ሲሉ እንደ ኀዳሪና ማኅደር፣ ጽምረትን እንጂ ተዋሕዶን አይገልጡም፡፡ ተዋሕዶ ግን እንደ ነፍስና ሥጋ ነው፡፡ ‹‹እያንዳንዱ ባሕርይ የግብር ክልሉን ጠብቆ ይኖራል›› የሚለው በተዋሕዶ የቃል ገንዘብ ለሥጋ፣ የሥጋ ገንዘብ ለቃል መሆኑንና መገናዘቡን መወራረሱንም የሚጻረር ነው፤ ቅዱስ ቄርሎስ እንዲህ ይላል ‹‹እንቲአሁ ለቃል ኮነ ለሥጋ ወእንቲአሁ ለሥጋ ኮነ ለቃል፡፡›› ይህም ማለት ‹‹የቃል ገንዘብ ለሥጋ ሆነ፤ የሥጋም ገንዘብ ለቃል ሆነ፤›› ማለት ነው፡፡ ይህ ፍጹም ተዋሕዶን የሚያመለክት ነው፡፡ ስለዚህ ነው ሥግው ቃል በተዋሕዶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው የምንለው፡፡ የልዮንን ጦማርና የኬልቄዶንን ጉባኤ ውሳኔ በመከተል የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንና የግሪክ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ‹‹ክርስቶስ ሁለት ባሕርያት አንድ አካል አለው›› ይላሉ፡፡ በአገላለጽም ሁለቱ ባሕርያት የተዋሐዱት ያለ መቀላቀል፣ ያለ መለያየትና ያለ መለወጥ ነው ይላሉ፡፡ አንድ ባሕርይ ለማለት የፈሩት ወደ አውጣኪ ትምህርት ይወስደናል ብለው በመፍራት ነው፡፡ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ሁለቱ ባሕርያት (የሥጋና የመለኮት) ተዋሐዱ ስንል ‹‹ወረሰዮ አሐደ ምስለ መለኮቱ ዘእንበለ ቱስሕት ወኢትድምርት፣ ዘእንበለ ፍልጠት ወኢውላጤ›› (ያለ መቀላቀልና ያለ መጨመር፣ ያለ መለየትና ያለ መለወጥ ከመለኮቱ ጋር አንድ አደረገው፤) እንላለን፡፡ አባቶቻችን ያስተማሯት ርትዕት ሃይማኖታችንም ይህች ናት፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ የተወደዳችሁ የማኅበረ ቅዱሳን ድረ ገጽ ተከታታዮች፣ ይህ ጥናታዊ ጽሑፍ ለማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል መቅረቡንና በታኅሣሥ ወር ፳፻፱ ዓ.ም በታተመው ፳፬ኛ ዓመት ቍጥር ፰ ሐመር መጽሔት፣ ከገጽ ፰ – ፲፭ ለንባብ መብቃቱን ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡
47042
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%8C%8A%E1%8B%AE%E1%88%AD%E1%8C%8A%E1%88%B5%20%28%E1%88%B0%E1%88%9B%E1%8B%95%E1%89%B5%29
ቅዱስ ጊዮርጊስ (ሰማዕት)
ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ አንስጣቴዎስ (ዘሮንቶስ) ይባላል። እናቱም ቴዎብስታ ትባላለች የዘር ሐረግዋም ከፍልስጥኤም ወገን ነው ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ጥር ፪ ቀን ፪፻፸፯ ዓም ተወለደ የተወለደባትም ቦታ ቀጰዶቅያ ትባላለች። ቀጰዶቅያም በትንሹ ምሥራቃዊ እስያ(እንደዛሬ አጠራር መካከለኛው ምሥራቅ)ትገኛለች ከሮም ገናና መንግሥት በፊት በፋርስ መንግሥት ሥር ነበረች ። ጊዮርጊስም የፋርስ ሰማዕት የሚባለው በዚህ ምክኒያት እንደሆነ ይነገራል ይህችኑ ሀገር ግሪኮችና ሮማውያን በቀኝግዛት ይዘዋት እንደ ነበር ታሪክ ያብራራል ። በዚህ አኳኋን አንዳንድ ሰዎች ቅዱስ ጊዮርጊስን የግሪክ ተወላጅ ነው ሲሉ ሎችም ደግሞ የሮማ ተወላጅ ነው ይላሉ ጥቂቶችም የእንግሊዝ ዜጋ ነው ይላሉ ለዚህ ሁሉ ከአፈ ታሪክ በስተቀር ብዙ ጊዜ ተመራምሮ እስካሁን ድረስ በቂ ማስረጃ አልተገኘም። ከዚህም የተነሳ ጊዮርጊስ የዚህ ሀገር ተወላጅ የዚያኝው ሀገር ዜጋ ነው የሚል አነጋገር ቢሰጥ አያስደንቅም ምክኒያቱም የሥራ ሰውንና ጅግናን ማንም ሰው የሱ ዜጋ እንዲሆን ሰለሚፈልግ ነው ። ይሁን እንጂ በዚያን ዘመን ወታደርነት ተፈላጊ ሙያ ስለነበር ቅዱስ ጊዮርጊስም ወታደር ሆኖ ብዙ ጀብዱ ፈፅሟል በወጣትነቱም የውትድርናን ሥራ እንደሠራ በግሪክና በኮብትና በሶርያ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ተጽፏል ይልቁንም በመጽሐፈ ስንክሳርና በራሱ ገድል ተብራርቶ ይገኛል።ቅዱስ ጊዮርጊስ ለጥቂት ጊዜ በወታደርነት ከሠራ በኋላ የክርስቶስ ወታደር ሆኖ ቤተክርስቲያንን ያገለግል ጀመረ ። ከቅዱስ ጊዮርጊስ ድረገጾች አንዱ ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ ቅዱስ ጊዮርጊስ በድዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት በድዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግስት ስለ ክርስትና ሃይማኖት ብዙ ተጋድሎ አድርጓል። ወንጌልንም አስተምሮ ያላመኑ ሰዎችን ወደ ክርስትና እምነት መልሷል ገድሉ እንደሚለው ቢሩታይትን የተባለችውን ልጃገረድ ድራጎን ለተባለው አውሬ ግብር እንድትሆን ቀርባ ሳለች ዘንዶውን በጦር ወግቶ ገድሎ እሷን ከመበላት አድኗታል። ይህንንም ዘንዶ ሰዎች ሁሉ አምላክ አድርገው ስለሚያመልኩት በተወሰነ ጊዜ አንዳንድ ከወንድም ከሴትም ወጣት እየመለመሉ ያቀርቡለት ነበር። አንዳንድ የቤተክርስቲያን ታሪክ ተንታኞች ግን በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ታሪክ አንዲት ልጃገረድን ከድራጎን እንዳዳነ የተመዘገበውን ጽሑፍ ልዩ ትርጉም ሰጥተውታል ። አባባላቸውም በዘመነ ሰማዕታት ፪፻፹ ዓ/ም-፫፻፭ ዓ/ም ድረስ በክርስቲያን ሴቶች ልጆች ላይ ብዚ ግፍ ይፈፀም ነበር ። ከዚያም የተነሣ አንድ ግፈኛ መኮንን በአንዲት ልጃገረድ ላይ ግፍ ሊፈፅምባት ሲሞክር ጊዮርጊስ ደርሶ ገድሎ ልጃገረዲቷን ከሞት አዳናት። ይህም ታሪክ በምሳሌያዊ አነጋገር ቀረበ ነገር ግን ከጊዮርጊስ ሥዕል ጋር የሚታየው ድራጎን በዓለም ላይ የሌለ አውሬ ነው ተብሎ ተገምቷል በግልጽ አነጋገር ዮሐንስ በራእዩ እንዳየው ዘንዶ ምሳሌያዊ መልክ ነው ማለታቸው ነው ። ይህንን አባባል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ብቻ ሳትሆን የግብፅ የአርመን የሶርያ የግሪክ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይቃወሙታል። ቅዲስ ጊዮርጊስ ድራጎኑን ከገደለ በኋላሥራው ባገር ሁሉ ታወቀ በዚያም ዘመን ክርስቲያኖች በየቀኑ እየተገደሉ በየሜዳው ይጣሉ ስለነበር በፈረሱ ጭኖ እየወሰደ እንዲቀበሩ ያደርግ ነበር።በሕይወት ያሉትንም እየተዘዋወረ ያጽናናቸውና በእምነታቸው እንዲተጉ ወንጌልን ያስተምራቸው ነበር። በተጭምሪም የግፍ ሞት ከሚፈፀምበት አደባባይ የደከሙትን ሽማግሌዎችንና አሮጊቶችን እንዳይፈጁ በፈረስ ወደ ሌላ ሥፍራ ያሸሻቸው ነበር ፈረሰኛው ጊዮርጊስ የሚሰኘውም በዚህ ምክንያት ነው። ስለ ክርስትና እምነት የተጻፉት የቤተክርስቲያን ንዋየ ቅዱሳትንም በየዋሻው መሬት እየቆፈረ ደብቆ በመቅበር ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፉ አድርጓል በጠቅላላ በተፈጥሮና በትምህርት ችሎታ በእግዚአብሔር ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተመላ ሰው ስለነበር ስለ እውነት ስለ ኢየሱስ ፍቅር ስለ ሰላም ስለ እኩልነት ስለ ፍትህ ተጋድሏል ይህም ሁሉ በቤተክርስቲያን ስጦታዊ ታሪክ ወርቃዊ ስጦታ ታእምራዊ ሰማዕት ተብሏል።በርግጥም ስለ እውነት ስለ ሰላም የሚመስክር ሰው ተአምረኛው ሊያሰኘው ይገባል። ይህም መንፈሳዊ ተጋድሎው ከ፪፻፷-፫፻፵ ዓ/ም የነበረው የቤተክርስቲያን አባት የሆነው አውሳብዮስ ዘቂሣርያ ቅዱስ ጊዮርጊስን ብርቱና ጠንካራ ሰማዕት እንደሆነ መስክሯል የአውሳብዮስ መጽሐፍ ፰-፲ ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ብዙ ዘመን ስለ እምነቱ ስለ ሀገሩ ነፃነት ስለ እኩልነት ስለ ሰላም ስለ ፍትህ ስለ ወንጌል መስፋፋት ስለ ቤተክርስቲያን ዕድገት ታማኝ ምስክርነትን በየአድባባየ እየመሰከረ ለሰባት ዓመታት ያህል እየታሰረ እየተሰቃየ እየተገረፈና እየተወገረ ጽኑ ተጋድሎ ከፈፀም በኋላ የመንፈስ ዐርበኝ እንደመሆኑ መጠን የመከራውን ሸለቆ ተሻግሮ ከሕይወት ወደብ ደርሶ ምእመናን እየተያዙ በሚገደሉበት በዱዲያኖስ ዘመን መንግሥት በ፫፻፫ ዓ/ም ሚያዝያ ፳፫ ቀን ልዳ በሚባለው ሀገር በሰማዕትንት ዐረፈ በዚህም ብዙ የታሪክ ጸሐፊዎች ተስማምተውበታል።ስለ ዜና ቅድስናው ከላይ በተገለፀው መሠረት ቅዱስነቱ ወይም ቅድስና ያለ ሥራ ሊሰጥ ባለመቻሉ ከነአውሳቢዮስ ዘመን ጀምሮ የቅዱስ ጊዮርጊስ የሥራ ታሪክ ጥናት ተጀመረ።ቅዱስ የተባለውን ስም ለማግኘት በሥራና በአካሄድ ክርስቶስን መምሰል እንደሱ ሌላውን ማገልገልና ለራስ ሳይሆን ሰለ ሌላው መኖር ያሻል ስለ ሌላው ተላልፎ መሞት መከራን መቀበል መሰቀልንም መሸከም በሰው ፊት መመስከርና ራስን መካድ ያስፈልጋል።< ቅዱስ ጊዮርጊስም ይህን ሁሉ ተግባር ሠርቶ በመገኘቱ ብዙ ምስክር ተገኝቶለት በ፮ኛው መቶ ዘመን በደቡብ ሶርያ በምትገኘው አድራ ወይም (ይድራስ) በተባለች ቤተክርስቲያን ተሰብስበው የቤተክርስቲያን አባቶች እውነተኛ ሰማዕትነቱንና ቅድስናውን በጉባኤ አጽድቀው ውሳኔውን ለሕዝብ አስተላልፈዋል።በ፩ሺህ፺፮ ዓ/ም ደግሞ በአንጾኪያ በትደርግው የሃይማኖት ጦርንት በራዕይ እንደታየ ተረጋግጦ ስመ ገናና መሆን ጀመረ ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ደሞ ማርያም ልጇን እየሱስ ክርስቶስን ይዛ በምትታይበት ስዕል ሥር "አክሊለ ፅጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀፀላ መንግሥቱ አንቲ ሁሉ ታስግዲ ሎቱ ወለኪሰ ይሰግድ ውእቱ" ተብሎ ይጻፋል ቅዱስ ጊዮርጊስ በእንግሊዝ አገር ቅዱስ ጊዮርጊስ በእንግሊዝ አገር ስመ ጥሩ ሰማዕት ነው ። "የእንግሊዝ መንግሥት ጠባቂ"በሚል የቅፅል ስም ይጠራል።ከ፰ኛው መቶ ዓ/ም ጀምሮ በእንግሊዝ አገር ዝነኛ እንደሆነ እንግሊዞች ያምናሉ በ፩ሺህ፷፩ዓ/ም ገድሉ በአንግሎ ሳክሶን ቋንቋ ተተረጎመ በዚሁ ዓ/ም በስሙ ቤተክርስቲያን ታነጸ በ፩ሺ፪፻፳፪ ዓ/ም ደግሞ በኦክስፎርድ በተደረገእ የሲኖዶስ ጉባኤ በዐሉ ከንኡሳን በዐላት ጋር ገብቶ እንዲቆጠር ተወሰነ ። በ፩ሺህ፫፻ ዓ/ም ፫ኛው ኤድዋርድ በነገሠ ጊዜ መደቡ ነጭ የሆነ ቀይ መስቀል ያለበት ባንዲራ ተሠርቶ የተጋዳዩ ጊዮርጊስ ባንዲራ ተባለ ይህም ለምድር ጦርና ለባሕር ኃይል መለያ እንዲሆን ተሰጠ የእንግሊዝ መንግሥት ጠባቂ በሚል እንደገና በ፩ሺህ፬፻፲፭ ዓ/ም በዐሉ ከዐበይት በዐላት ጋር እንዲቆጠር ተወሰነ ። ዛሬም ቢሆን በእንግሊዝ ቤተክርስቲያን የዘውትር የጸሎት መጻሐፍ ላይ የሚገኘውን ኮመንተሪ የበዓላትም ቀን መቁጠሪያ ካላንደር ሚያዚያ ፳፫ ቀን የቅደስ ጊዮርጊስ ዕረፍት መታሰቢያ ዕለት እንደሆነ ያመለክታል ለዕለቱም ተስማሚ የሆነ ምንባብና መዥሙር በዚሁ የጸሎትም መጻሐፋቸው ተዘጋጅቷል ። ይሁን እንጂ አከባበሩ ሥራ ፈቶ በመዋል ሳይሆን ከመንፈሳዊ ሥራቸው ጎን የዕለት ተግባራቸውንም በማከናወን በዐሉን በደመቀ ሁኔታ ያከብራሉ በዚያም ሆነ በዚህ ቅዱስ ጊዮርጊስ በእንግሊዝ አገር ታላቅ አክብሮት ያለው ሰማዕት ነው ። የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በህንፃው አሠራርም ሆነ በውስጣዊ ድርጅቱ መሟላት በካህናት ብዛት ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ገዳማትና አድባራት እጅግ የላቅነው እንዲሁም በኦክስፎርድ በሰሜን አይርላንድና በእስኮትላንድ የሚገኙት ታላላቅ ካቴድራሎች ለቅዱስ ጊዮርጊስ መታሰቢያነት የተሰየሙ ናቸው።በእንግሊዝ የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብር ከሌሎች ቅዱሳን የላቀና የተወደደ ሆኖ እናገኘዋለን ። ከላይ የተገለጸው የቅዱስ ጊዮርጊስ ታሪክ የተገኘው: ፩ኛ/ ዲክሽነሪ ኦፍ ክርስቲያ ባዮግራፊ ቮልዩም ፪ኛ ከ፭፻፵፭-፮፻፵፰። ፪ኛ/ ኢንሳይሎፔድያ ብሪታኒካ ገጽ ፯፻፷፰ ፫ኛ/ ኦክስፎርድ ዲክሽነሪ ዘቤተ ክርስቲያን፬ኛ/ ከሚስተር ዴቪድ እስኪዩት'' የታሪክ ፕሮፌሰር ማስታወሻ። እነዚህ መጻሕፍት ታሪኩን ከማብራራት በቀር ቅዱስ ጊዮርጊስ የእንግሊዝ ዜጋ ነው አይሉም። ቅዱስ ጊዮርጊስ በኢትዮጵያ ቅዱስ ጊዮርጊስ በክርስቲያን አገሮች ሁሉ የታወቀ እንደመሆኑ በኢትዮጵያም ታዋቂ ስመጥር ሰማዕት ነው። ወደ ኢትዮጵያ ጽላቱ የገባው ብ፲፫ኛው ክፍለ ዘመን በዐፄ ዐምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት እንደነበር ከክብረ ነገሥት መረዳት ይቻላል ። በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳም ውስጥ ብዙ ዐመታት የኖሩ አባ ልዑለ ቃል የተባሉ መነኩሴ ከሶርያ ደብረ ይድራስ ከሚባለው ገዳም የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት ከገድሉ ጋር አምጥተው ለዐፄ አምደ ጽዮን አስረከቡ ዐፄውም ቤተ ክርስቲያን አሠራለት ገድሉም ከዐረብኛ ወደ ግእዝ ተተርጎመ ። ዐምደ ጽዮንም የጊዮርጊስን ጽላት አስይዞ ከጠላቶቹ ጋር በመግጠም አሥር ታላላቅ ዘመቻዎችን በድል አድርጊንት ተወቷል ። ከአንዳንድ የታሪክ ዘጋቢዎች እንደተገለጸው ዐፄ አምደ ጽዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ አማላጄና ረዳቴ ስለሆነ አረመኔዎች ድል ሊያደርጉኝ አይችሉም እያለ በቅዱስ ጊዮርጊስ አማላጅነትና ረዳትነት አብዝቶ ያምን ነበር። በዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ዘመንም ቢሆን በጥንታዊ ታሪክ እንደተገለጸው በዶዎሮ ክፍለ ሀገር አርዌ በድላይ የተባለ የአረመኔዎች መሪ የነበረ ብዙ ወታደሮች ሰብስቦ ዘርዓ ያዕቆብን ሊወጋው ተነሥ ። ዓፄ ዘርአ ያዕቆብም የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት ይዞ ሠራዊቱን አስከትቶ ዘመተና ጠላቱን ድል መቶ ተመለሰ ። ይህንንም የዘርዓ ያዕቆብ ጸሐፊ ትእዛዝ የነበረው መርቆርዮስ ከዘርዓ ያዕቆብ ታሪክ ጋር መዝግቦታል ። ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ነገሥታት በሚዝምቱበት ታላላቅ ዠመቻዎች ሁሉ የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት ትተው አይንቀሳቀሱም ነበር ። ይህንን እውነት ለማረጋገጥ ቢፈለግ በዐድዋ ላይ ከኢጣልያ ጦር ጋር በተደረገው ውግያ ማለትም የአድዋ ጦርነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረገው ታአምራዊ ተሳትፎ ኢትዮጵያን በዓለም ታሪክ በጦር ኃይል ፲ጊዜ እጥፍ የሚበልጣትን አገር አሸንፋ ታዋቂ የነፃነት አገር እንድትባል ያደረጋትን ታሪክ መመልከት ይበቃል ። ይህም ዳግማዊ ዓፄ ምኒሊክወደ ዐድዋ ሲዘምቱ በአራዳ ገነተ ጽጌ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘውን የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት አስይዘው ዘመቱ ። ጦርነቱም እንደተጀመረ ቅዱስ ጊዮርጊስ የእርዳታ እጁን ዘረጋ በዛም ጊዜ ብዙ የጠላት ሠራዊት አለቀ ። ጠላትም እንደመሰከረው አንድ በነጭ ፈረስ ላይ የተቀመጠ ጅግና ነው የፈጀን ብለዋል በወቅቱ የነበረ አንድ የኢጣልይ ጋዜጠኛ ወደ አገሩ ባስተላለፈው ዘገባ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ሠራዊት ጎን ተሠልፎ የኢጣሊያን ሠራዊት አርበደበደው የምንዋጋው ከሰው ጋር ብቻ ሳይሆን ከእግዚአብሔርም ጋር ሰለሆነ በጦርነት ድል ልንመታ ችለናል ሲል አስተላልፏል ። በዚህም የተነሣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነቱን ፈጥኖ ደራሽነቱን ስለት ሰሚነቱን አማላጅነቱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን ስለሚያምኑበትና ስለሚወዱት ጽላቱ በተተከለበት ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራበት በዓሉ በሚከበርበት ስሙ በሚጠራበት ሥፍራ ሀሉ እየተገኙ በጸሎትና በምስጋና ያስቡታል ፍጡነ ረድኤት ነውና ። ተጨማሪ መረጃ ቅዱስ ጊዮርጊስ (272-295 ዓም) በታሪካዊ ሰነዶች መሠረት በሮሜ መንግሥት በቄሣሩ ዲዮክሌቲያን ዘመን የነበረ አንድ ክርስቲያን ወታደር ነበር። በዚህ ዘመን ክርስትና በሮሜ መንግሥት ሕግጋት ተከለከለ። ግን በሕዝቡ ዘንድ እንዲሁም በወታደሮች ዘንድ ወንጌል እየተስፋፋ ነበር። በ295 ዓም በዲዮክሌቲያን ትዕዛዝ ወታደሮች ሁሉ ኢየሱስን ለመካድ፣ ለአረመኔ ጣኦት ለመሠው፣ ወይም ለመገደል ተገደዱ። ጊዮርጊስ የተወደደ መኮንንና የንጉሥ ወታደር ሲሆን ለንጉሡ ፊት እምቢ አለው። ስለዚህ እጅግ አሰቃዩት፣ ሆኖም እስከ ሞቱ ድረስ ኢየሱስን ከቶ አልካደም። ነገር ግን በዚህ ወቅት ብዙ የዋሆች ወንዶችም ሴቶችም በገሃድ ተሰቃዩና የሰዎች ስሜት ከንጉሦቹ ጨካኝ ሃይማኖት ወደ ክርስትና በጅምላ እየተዛወረ ነበር። ከጥቂት አመታት በሗላ ክርስትና በሕግ ተፈቀደ፤ በመቶ ዘመን ውስጥ ክርስትና ብቻ በሮማ የመንግሥት ሃይማኖት ሆነ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደ ሄሊዮ ሶል ኢንሲኩስ ተደርጎ የተገለጸ ሲሆን የመጨረሻው ጳጳስ ጆርጆ ማሪዮ ፍራንቸስኮ በርጎሊዮ የሰማዕትነት መልአክ በመሆን በቫቲካን ይፈራ ነበር ። ከዚህ በኋላ የጊዮርጊስ ስም በክርስቲያኖች ዘንድ በጣም ዘመናዊ ሆነ፤ በክርስትና እስካሁን ብዙ ቀሳውስት እና ምእመናን «ጊዮርጊስ» ተብለዋል። ከዚህ በላይ እንደ ብዙ አገራት አቃቤ በልማድ ይቆጠራል። የክርስቲያኑን ወታደር የጊዮርጊስን ታሪክ ትዝ ሲሉ፣ ከሌሎች ጥንታዊ አፈ ታሪኮች ጋራ ተዛበ፤ ስለዚህ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዘንዶ በመግደል ሳዱላን አዳነ በማለት ጨምረዋልና ይህ አፈ ታሪክ በመላው ዓለም ተሰማ። ዳሩ ግን ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚታወቀው በቤይሩት አገር በየተወሰነ ጊዜ ስው የሚገበርለትን ዘንዶ በመግደሉ ነው። የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በቀይ መስቀል ዳግመኛ እንዲወለድ ተደርጎ የተሠራ ሲሆን እና የኢየሱስ ክርስቶስ የጋሮጅዮ እህት እሽት በሌሊት በጨለማ ውስጥ በሚታየው እውነተኛ ህይወት ማእዘናዎች ሌሊት ሁሉም ወንዶች በጨለማ እና በሙታን ነቅተዋል, እናም ኢየሱስ የዱር ገዳይን መገደሉን በፋሲካ እንቁላሎች እና በኢየሱስ ምትክ የኢየሱስ ወንጌላት በሚገኙ ወንጌላት መሠረት በመላው አለም የስፕ ሾላ የመሰለ እንቁላል ውስጥ በታዋቂ የክርስቶስ ደቀመዝሙሮች ውስጥ ተነስቷል። ጊዮርጊስ ዘንዶውን ስለ መግደሉ መጀመርያ የተጻፈው በአንድ ጅዮርጅኛ ጽሁፍ ከ1050 ዓም ገደማ ነበር። እንዲሁም በዚያን ወቅት ጊዮርጊስ ዘንዶውን ሲገድል የሚያሳዩ ምስሎች በክርስቲያናዊ ሥነ ጥበብ በሰፊ ይታዩ ጀመር። ይህም በተለይ ከጅዮርጅያና አናቶሊያ ተስፋፋ። ሆኖም ከ1050 ዓም አስቀድሞ በወጣው ሥነ ጥበብ ዘንድ፣ ጊዮርጊስ ሳይሆን ሌላ በ295 ዓም የተገደለ ክርስቲያን ሰማዕት ቅዱስ ቴዎድሮስ ቲሮ ዘንዶውን እንደ ገደለ የሚል ተመሳሳይ ትውፊት ይታወቅ ነበር። በማኒኪስም ተጽእኖ በኩል፣ በአለም ፍጥረት የዘንዶ ውግያ እንደ ተከሰተ የሚሉ የባቢሎን፣ የግብጽ ወይም የፋርስ አረመኔ እምነቶች ቀርተው ፣ እንደ ተስፋፉ ይታያል። የሮሜ መንግሥት
12200
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B4%E1%88%9E%E1%8A%AD%E1%88%AB%E1%88%B2
ዴሞክራሲ
ዴሞክራሲ የፖለቲካ ሥርዓት ሲሆን ትርጓሜውም ሕዝባዊ መንግስት ማለት ነው። በሌላ አባባል ዲሞክራሲ ማለት ህዝብ የሚያስተዳድረውን አካል ያለምንም ተፅዕኖ ከመካከሉ መርጦ ሥልጣን የሚሰጥበት ሥርዓት ነው። ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆነ ዴሞክራሲ በተጠነሰሰበት ጥንታዊት ግሪክ ፣ ሰዎች ይኖሩ የነበረበት መሠረታዊ የፖለቲካ አሃድ (ዩኒት) ፣ ከተማዊ መንግስት ይባላል። ይህ በአሁን ዘመን ካለው አገር ወይንም ብሔራዊ መንግስት ይለያል። ከተማዊ መንግስታት፣ ለምሳሌ አቴና እንደ ከተማ አስተዳደርነቱ ፣ በቆዳ ስፋት አንስተኛ ስለነበር የዘመኑ ዲሞክራሲ በቀጥተኛ ተሳትፎ (በስብሰባ) ላይ የተመሰረተ ነበር። ነገር ግን ይህ ዓይነት አሰራር ከ፲፯ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ ለተነሱት በንፅፅር ግዙፍ ለሆኑት ብሔረ መንግስታት እማይቻል ስለነበር (ማለት ከአገሪቱ ግዙፍ የቆዳ ስፋት አንጻር ሁሉን ዜጋ በየሳምንቱ ለስብሰባ መጥራት ስለማይቻል) በእንግሊዝ አገር ፓርላማ የተባለ አዲስ ሥርዓት ተፈጠረ። ይህም ማለት ሕዝቡ ተወካዮቹን (የፓርላማ ዓባላትን) ይመርጣል፤ ተመራጮችም መንግሥትን ይመሠርታሉ። ይህ ዓይነት ሥርዓት (ቀጥተኛ ያልሆነ ዴሞክራሲ) በመባል ይታዎቃል። በአሁኑ ሰአት አብዛሃኛዎቹ የአለም ሃገራት የሚጠቀሙበት የመንግስት መዋቅር ነው። ዜግነትና ዴሞክራሲ አንድ ሥርዓት ዲሞክራሲያዊ፣ በሌላ አነጋገግር ከሕዝብ ወይም በሕዝብ የቆመ ነው ከተባለ፣ ሕዝብ ማለት እዚህ ላይ ምንድን ነው? አብዛኛውን ጊዜ ሕዝብ ማለት ዜጋ ማለትን ሲዎክል፣ እስከ ሃያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ አብዛኞች ዲሞክራሲያዊ ሃገሮች ዜግነትን ትንሽ ለሆነ የህብረተሰብ ክፍል (ሴቶችን፣ ድሆችን፣ ዘሮችን ያገለሉ) ብቻ ያድሉ ነበር። እነዚህ ትንሽ ክፍሎች ብቻ እሚሳተፉበት ዴሞክራሲ በአሁኑ ዘመን ተቀባይነትን ያጣ ነው። ባሁኑ ዘመን፣ ዲሞክራሲ ማለት ብዙኃኑ ኅብረተሰብ መንግሥት የማዋቀር መብት አለው። የጥቂቶች መብት ደግሞ በህግ የተጠበቀ ነው። ሥርዓተ ሕዝብ፣ ሥርዓተ ልሂቅ፣ ሥርዓተ ጥቂት ፖለቲካዊ ዜግነት ሕጻናትን እንደማይጨምር አሁን ድረስ አብዛኞች ሃገራት የሚሰሩበት ነው። ይሁንና፣ በዚህ መንገድ አላግባብ ሌሎችም የሕዝብ አካላት እየተገለሉ ሄደው፣ ዴሞክራሲው ወደ ሌላ ዓይነት ሥርዓት ሊቀየር ይችላል። ለምሳሌ በህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ የተከበሩ ሰዎች ብቻ እሚሳተፉበት ሥርዓት ሲፈጠር ሥርዓተ ልሂቅ ወይንም አሪስቶክራሲ ይባላል። በሆነ አጋጣሚ ዕድል አግኝተው ጥቂት ቡድኖች ብቻ በማህበረሰቡ ላይ በሚተላለፉ ውሳኔዎች ሲሳተፉ ሥርዓተ ጥቂት ወይንም ኦሊጋርኪ ይባላል። ይህን ሁኔታ ለማዎቅ አንድ አንድ ጊዜ አስቸጋሪ ይሆናል ምክንያቱም ሙሉ በሙሉ ዴሞክራሲያዊ በሆነ ሥርዓት ሳይቀር፣ ጊዜ አግኝተው በፖለቲካው የሚሳተፉ ግለሰቦች ከአጠቃላይ ዜጋ ጥቂት ስለሆኑ። ይሁንና በዲሞክራሲ፣ የመሳተፍ መብቱ ለሁሉም ዜጋ ምንጊዜም ያለ ነው፣ ይጠቀሙበት አይጠቀሙበት። ዴሞክራሲ ለምን ተፈለገ? እንደ ፈላስፋው ጆን ስቱዋርት ሚል ሦስት ምክንያቶች ይጠቀሳሉ፦ ሥልታዊ ምክንያት ሕግ አርቃቂዎች የአንድን ሕብረተሰብ ጥቅም፣ መብት እና አስተሳሰብ በሚያረቁት ሕግ ውስጥ ግምት እንዲያስገቡ ከሌሎች የፖለቲካ ሥር ዓቶች በላይ ዴሞክራሲ ያስገድዳቸዋል። በዚህ ምክንያት ሰዎች በዚህ ሥርዓት ውስጥ የመጎዳታቸው ዕድል አንስተኛ ነው። ተመራማሪ ዓማርትያ ሴን ዋቢ ሲሰጥ «በማናቸው ዲሞክራሲያዊና ሉዓላዊ መንግስታት ከፍተኛ ርሃብ ተከስቶ አያቅም» ይላል። ሥነ ዕውቀታዊ ምክንያት ዴሞክራሲ አብዛኛውን ሕዝብ በውሳኔ አስጣጥ ላይ ስለሚያካፍል፣ ከሌሎች የፓለቲካ ሥርዓቶች በበለጠ ሥለ ሕዝቡ ጉዳይ ያዎቀ ሆኖ ይገኛል። በውሳኔ አሰጣጥ የሚካፈለው ሕዝብ መብዛት በሌላ ጎን ትክክለኛ ውሳኔ ላይ ለመድረስ እሚደረገውን ስራ ያግዛል፣ ተሳታፊዎችም ስለ ጉዳዮች የበለጠ የተተቸና የተብራራ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ይረዳል። የዜጎችን ባሕርይ የማሻሻል ምክንያት በዴሞክራሲ ሥርዓት ያሉ ሰዎች በውሳኔዎች ላይ ስለሚሳተፉ፤ ከሌሎች ሥርዓት ሰዎች በተለየ እራሳቸውን ችለው እንዲያስቡ፣ በሃሳባቸው ምክንያታዊ እንዲሆኑ እና የሌሎችን መብቶች ግምት ውስጥ እንዲያስገቡ ስለሚገደዱ በሥነ ምግባር እንዲሻሻሉ ይሆናሉ። ከሚያስከትለው ጥቅም ውጭ ሌሎች ሥነ ምግባራዊ ጥቅሞች ይጠቀሳሉ። ለምሳሌ ሓርነት እና ዕኩልነት፣ እኩልነት፣ የሕግ የበላይነት፣ የመናገር መብት፣ ፍትህ ይጠቀሳሉ በዴሞክራሲ ላይ የተነሱ ትችቶች ፕላቶ የሥርዓተ ልሂቃን ዓይነት መንግስት ደጋፊ ስለነበር ዲሞክራሲን ከዚህ አቋሙ ተነስቶ ለመንቀፍ ሞክሯል። በእርሱ አስተሳሰብ በዲሞክራሲ ሥር ዓት ወደ ሥልጣን ላይ መውጣት እሚችሉት የምርጫ ሥር ዓቱን በማጭበርበር ወይንም በብልጥ ንግግር እና ስራ ሰውን በማታለል የተካኑ ሰዎች ይሆናሉ። ምርጫን እሚያሸንፉ ሰዎች ደግሞ የግዴታ መንግስታዊ ኣስተዳደር ላይ ብቁ ሆነው ስለማይገኙ፣ ዴሞክራሲ መንግስትን ለንደዚህ ያለ ግሽበት ይዳርጋል ይላል። የእንግሊዙ ቶማስ ሆብስ በአንጻሩ የዘውድ ሥርዓትን በመደገፍ፤ የዴሞክራሲ ሥርዓት መንግስት እንዳይረጋጋ እሚያረጉ ተቃውሞዎችን ያበረታታል በማለት ይነቅፋል። የዴሞክራሲ ተቋሞች ምርጫ ተቋም ዴሞክራሲ የመጣው የግሪክ ቃል ከሆኑት «ዴሞስ» ማለት «ህዝብ» እና «ክራቶስ» ማለት «ስልጣን» የመጣ ቃል ነው። በጥንታዊ የግሪክ ከተማ አቴንስ አገዛዝ ይተገበር ነበር። ዋቢ ጽሑፎች የፖለቲካ ጥናት
17036
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%20%E1%88%99%E1%8B%9A%E1%89%83
የኢትዮጵያ ሙዚቃ
በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ጊዜ የመጀመሪያውን ግራማፎን ወይም የሸክላ ማጫወቻ በ፲፰፻፹፱ ዓ.ም. ሄንሪ ደ አርሊንስ እና ኒኮላስ ሊዋንቲቭ ለዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አመጡላቸው። ይኸውም ማጫወት ብቻ እንጂ ድምጽ አይቀዳም ነበር። በኋላ ግን በዓመቱ በ፲፱፻፺ ዓ.ም. ከንግሥት ቪክቶሪያ የተላኩ የእንግሊዝ መልዕክተኞች በመጡ ጊዜ ግራማፎኑንና ድምፅ መቅጃውን ይዘውላቸው መጡ። ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፃቸው በዲስክ የተቀረፁት ዓፄ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ናቸው። ዛሬ በእንግሊዝ አገር በለንደን ከተማ ብሪቲሽ ኢንስቲቲውት ኦፍ ሪኮርድ ሳውንድ በተባለው ሙዚየም ውስጥ ይገኛል። በሸክላ ቀረፃ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ በሸክላ የተቀረፀው የመጀመሪያው ዜማ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ስራዎች ሲሆኑ ዘመኑም በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ነበር። ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ በጀርመን ቆይታቸው ወቅት የጀርመን የሙዚቃ ድርጅት ጠይቋቸው የኢትዮጵያ መዲናና ዘለሰኛ ዜማዎች በ፲፯ አይነት ስልት እየተጫወቱ ተቀርፀዋል። ኩባንያው የተሰማ እሸቴን ዜማዎች በ፲፯ ሸክላዎች የቀረፀው ሲሆን ለዜማው ባለቤት የድካም ዋጋ እንዲሆን በወቅቱ ፲፯ ሺህ የጀርመን ማርክ ከፍሏቸዋል። በዘመኑ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያም አሁንም እነዚህ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ብርቅዬ ሸክላዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ። እነዚህ በተቋሙ እጅ ያሉት ፲፮ ሸክላዎች እያንዳንዳቸው ሁለት ዜማዎችን የያዙ ሲሆኑ ባጠቃላይ ፴፪ ዜማዎች ተቀርፀውባቸዋል። እያንዳንዱ የሸክላው ገፅ ላይ ወይም ተብሎ ተሰይሟል፣ የዜማው ስም ተፅፎበታል፣ የዜማው ባለቤት ተሰማ እሸቴ ስም አለ፣ ሸክላው ጀርመን ሀገር መሰራቱ እንዲሁም የሸክላው ቁጥር ተጠቅሷል። በ፲፱፻፳፭-፳፮ ዓ.ም. አካባቢ የእነ ፈረደ ጎላ፣ ንጋቷ ከልካይና ተሻለ መንግሥቱ የዜማ ሸክላዎች ብቅ እስከሚሉ ድረስ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ሸክላዎች ከ፳ ዓመታት በላይ አቅም ባላቸው ቤተሰቦች ዘንድ በብቸኝነት በግራማፎን ሲደመጡ ቆይተዋል። በቀ.ኃ.ሥ. ጊዜ ግርማዊ ጃንሆይ በአልጋ ወራሽነታቸው በ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. አውሮፓን ጎብኝተው ሲመለሱ አርባ የአርመን ተወላጆች በበጎ አድራጎት ለመርዳት ካስመጧቸው የመንፈስ ማነቃቂያና የሞራል መጠበቂያ እንዲሁም ለሀገሪቱ የሥልጣኔ እርምጃ ይጠቅማል በማለት የሙዚቃ ትምህርት ቤት አቋቋሙ። ከዚህ በኋላ በዚሁ ዓመተ ምሕረት ከወለጋ ጠቅላይ ግዛት ከሾጎሌ ፻፳ የሚሆኑ ወጣቶች መጥተው በሙዚቃ ትምህርት እንዲሰለጥኑ ተደርጎ በ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. የግርማዊ ጃንሆይ ንግሥ በዓል በነዚሁ ሙዚቀኞች ተከብሮ ውሏል። እነዚህ የመጀመሪያው ኢትዮጵያውያን ሙዚቀኞች በጣሊያን ወረራ ጊዜ ግማሾቹ ሲገደሉ የቀሩትም ተበታትነዋል። የኢትዮጵያ ነፃነት እንደተመለሰ ይኸው የሙዚቃ ክፍል ድርጅት አስፈላጊ በመሆኑ ከመስከረም ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፬ ዓ.ም. ጀምሮ እንደገና እንዲቋቋም በግርማዊ ጃንሆይ ትዕዛዝ ተሰጥቶ ከጣሊያን ወረራ በፊት በቦይስካውትና በየትምህርት ቤቱ የሙዚቃ ትምህርት የጀመሩ ስለነበሩ ተመርጠው በካፒቴን ኬቮርክ ናልባንዲያን አስተማሪነት ሥራው በክቡር ዘበኛ ድርጅት ውስጥ ተጀመረ። በኢትዮጵያ የሙዚቃ ሥልጣኔ የተስፋፋውና የተጀመረው ከውጭ ሀገር የሙዚቃ መምህራንን በማስመጣት በክቡር ዘበኛ ሙዚቃ ክፍል ሲሆን ለዚሁ ክፍል ከሰለጠኑት ብዙዎቹ በልዩ ልዩ ድርጅቶች ውስጥ በመሰማራት የሀገራቸውን ወጣቶች በሙዚቃ ጥበብ በማሰልጠን ላይ ይገኛሉ። ከዚህም በተረፈ ድርጅቱ ያሰለጠናቸውን የሙዚቃ አዋቂዎች በ፲፱፻፴፭ ዓ.ም. ወደ ምድር ጦር ሙዚቃ ክፍል እየላከ እንዲያስተምሩ አድርጓል። በ፲፱፻፴፯ ዓ.ም. የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት አሁን የቀ.ኃ.ሥ. ቲያትር ክፍል የተባለው ተቋቁሞ ቲያትር በሚታይበት ጊዜ የክብር ዘበኛ ሙዚቃ ክፍል ረድቷል። የክብር ዘበኛ ሙዚቀኛ ክፍል በግርማዊ ቀ.ኃ.ሥ. መልካም አሳቢነት ከ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. ሥራውን ከወጠነበት ቀን ጀምሮ የተጣለበትን አደራ በሚገባ ያከናወነ ለመሆኑ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን ክፍሎች የረዳ ከመሆኑም በላይ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የአማርኛ ሙዚቃን አራቆ በመቀመር ለሌሎች ሁሉ መልካም አርአያ ሆኖ የኢትዮጵያ ዜማ ከሀገሩ አልፎ በሌላው ዓለም እንዲታወቅ አድርጓል። በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. በቀ.ኃ.ሥ. ቲያትር ቤት በተደረገው የሙዚቃ ውድድር የክ/ዘ ሙዚቃና ቲያትር ክፍል ፩ኛ ሆኖ የተሸለመ ከመሆኑም በላይ እስከ ዛሬ ድረስ ሌላ ውድድር ስላልተደረገ የከፍተኛነቱን ደረጃ አሁንም እንደያዘ ነው። ተዛማጅ መጣጥፎች የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መሣሪያዎች ዋቢ ምንጮች ናሽናል ቢብሊዮግራፊ ቡድን፣ የአንጋፋ አርቲስቶች መዝገበ የሕይወት ታሪክ፣ መጋቢት ፳፻ የኢትዮጵያ ታሪክ
46259
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A4%E1%88%B2%20%E1%8A%A5%E1%8A%93%20%E1%8B%A8%E1%8B%B2%E1%88%B2%20%E1%88%B2%E1%88%B0%E1%89%B0%E1%88%9E%E1%89%BD%20%E1%8D%8D%E1%88%8D%E1%88%9A%E1%8B%AB
የኤሲ እና የዲሲ ሲሰተሞች ፍልሚያ
የኤልክትሪክ ኃይልን ለመብራት አገልግሎት ለማዋል የኤሲ እና የዲሲ ሲሰተሞች ፍልሚያ እና እድገቱ የኤሲ(ተለዋዋጭ ጅረት) እና የዲሲ(ቀጥተኛ ዥረት ወይንም ኮረንቲ) ሲሰተሞች ፍልሚያ ተብሎ የሚታወቀው በ 1880ዎቹ እ.ኤ.አ. የእነዚህ ተወዳዳሪ የኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መንገዶች ዘዴ፤ ማለትም ኢንካነዴሰንት ወይንም አሸብራቂ መብራት ከቀጥተኛ የኤሌክትሪክ ከረንት በታዋቂው ተመራማሪ እና የንግድ ሰው ቶማስ ኤዲሰን እና የአርክ መብራት ከተለዋዋጭ የ ኤሌክትሪክ ከረንት በሌላው መሀንዲስ እና የፈጠራ ሰው ጆርጅ ዌስቲነገሀውስ፤ የደምበኛ ማግኘት፤መያዝ እና መመረጥ ፤ የሲሰተሙ ደህንነት፣እናም ከህዝቡ፣ ከመንግስት እናም እርስ በርስ ያላቸው የፈጠራ መብት ጉዳይ ብሎም የእሌክትሪክ ኃይል አምራች ድርጅቶቻቸው እና የሲስተሞቻቸውንም እድገትን ያጠቃልላል፡፡ በቴሌግራፍ ገኝት ዘመን ወቅት ሀምፍሬይ ዴቭ የተባለው እንግሊዛዊ የኬሚስትሪ ሰው የሁለት ሽቦዎችን ጫፍ በቻርኮል ወይንም ካርቦን ሽቦ በማያያዝ ሌላኛውን የሽቦ ጫፍ በባተሪ ሲያግለው ግሎም አርክ መብራት() ተባለውን ግኝት አስገኘ፤ ጆሴፍ ስዋን የተባለውም እንገሊዛዊ በ1950 አካባቢ ቫኪውም በሆነ አምፖል ውስጥ ሙከራ አድርጎበት ነበር፤ ይሁን እና ይህን ግኝት ለኤሌክትሪክ መብራት ጥቅም እንዲሰጥ አድርገው አልቀረፁትም ነበር፡፡ ቶማስ ኤዲሰን ( በ1878 ሳይንቲስቱ ቶማስ ኤዲሰን ወደ ስራ ቦታዎች ፤ የንግድ፤እና የመኖሪያ ቤቶች የኤሌክትክ ብርሀን የመስጠት እና የማከፋፈል ገበያ ጥሩ መሆኑን ተረዳ፤ ይህም በአርክ የኤሌክትሪክ ብረሀን ከፍተኛ ሀይል ያለው መብራት ሰፋ ያለ ስፍራን እንደ መንገድን ለማብራት ይጠቀሙበት ስለነበረ ነው፡፡ ስለዚህም ኤዲሰን እንደዚህ ብሎ ወደ ገበያው ገባ (ኤሌክትሪሲቲን ዋጋውን ዝቅተኛ በማድረግ ለብዙሃኑ እናዳርሳለን በዚህም ሻማን የቅንጦት እናደርጋለን)" ስለዚህም በ 1882 ኤዲሰን ኢሉሚናቲንግ ካምፓኔ የሚባል ድርጅቱን ከፈተ ስለዚህም ኢንካነዴሰንት አምፖል በመጠቀም በ110ቮ አድርጎ ዘዴውን ቀረፀ፤ በዚህም የመብት ማስከበሪያ ሰነዱን ንግድ ፍቃዱን ከገኘ በሆል የዘዴውን ጥገናም ሆነ ማደግ ተቆጣጠረው፤ለዚህም የክፍያ መቆጣጠሪያ በግልጋሎቱ ልክ የሚቆጥር መለኪያ ሜትርንም አብሮ ፈለሰፈ፤ ይህ ቀጥተኛ የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጫ ችግር ጊዜ ከኃይል አጠራቃሚ ምንጭ መስጠቱ፤ኃይል ማመንጫው ወይንም ባትሪው በቀላሉ ከሌላ ጋር መቀጠል መቻሉ ለማስፋፋት ወይንም ፍላጎት ሲቀንስ፤ ይሁን እና ለአጭ ር ርቀት ብቻ የሚሆን የኤሌክትሪክ ሀይል ማስተላለፍ መቻሉ እና ለሩቅ ስፍራዎች ማመንጫ ጣቢያዎቹን እዛው ለምሳሌ ከተማ መሀል መገንባት ማስፈለጉ የዘዴው ድክመቶች ወይንም መሻሻል የሚገባቸው አሰራሮች ነበሩ፡፡ የኤዲሰን ተፎካካሪ ዲሲ ያለበት መዳረሻዎችንም ጭምር ኤሲ በማስራጨት ጀመረ፤ የኤዲሰን ዘዴ ወፍራማ የኮፐር ሽቦ መጠቀሙ ወጪው ከፍተኛ ከመዳረጉ ባሸገር የኤዲሰን ዲሲ ዘዴ የከተሞችን ጨረታ ማጣት ጀመረ፤ በዚም የኤዲሰን አማካሪዎች እና ተቀጣሪዎች ከትላልቅ ከተሞች በስተቀር የእነሱ ዘዴ ተመራጭት እንደማይኖረው ስለዚህም ወደ ኤሲ ገበያ እንዲቡ ቢያስቡም ኤዲሰን ተቃወመው፤ ኤዲሰን ያለው አቆሙ ላይ የፀናው የከፍተኛ ቮልቴጅ ሞት ከማስከተሉ አንፃር እና የሴፍቲ ዘዴዎችንም ለማበልፀግ ገና ረዥም ጊዜ ይወስዳልብሎ ስላመነ ነበር፤ ስለዚህም ምንአልባትም ኤልክተሪክ ለዚህ አይነተ ጥቅም ላይ እንዳይውል በመንግስት ይከለከላል የሚል አስተሳሰብም የያዘ ነበር፤ ስለዚህም ከኤዲሰን ድርጅት እቃ የሚገዙትን እነ ዌስቲንግስተን እና ቶሆምሶን ጨምሮ በመብት ሰነዶች ጉዳይ ጋርም ብዙ አድክሞቸዋል ፤ በኤዲሰን የዲሲ ማከፋፈያ ዘዴ ከማመንጫ ጣቢያው የሚወጣውን ኃይል በወፋፍራም ሽቦዎች ወደ የፋብሪካ ሞተሮች እና ለደንበኛች መብራት የተቀጠሉ ነበሩ፣ በአንድ እና ተመሳሳይ የቮልቴጅ ኃይል መጠንም ነበር የሚዳረሰው ይህም የካረቦኑ (የፊላመንት) ኢንካንዲሰንት ሽቦ በዚህው ኃይል እንዲበራ ተደርጎ ስለሚፈበረክ ነበር፡፡ ጆርጅ ዌስቲነገሀውስ ( በ1884 የሰሜን አሜሪካው ባለሀብት እና ተመራመሪጆ ዌስቲንግሀውስ ወደ ኤሌክትሪከ ብርሀነ ገበያው ገባ ፤በመጀመረያም የኤዲሰን የዲሲ ሌላኛው ተፎካካሪ ሆኖ ነበረ ነገር ግን በአውሮፓ መፅሄት ዩ.ኬ. የኤንጂነሪንግ ቴክኒክ ያነበበውን የኤሲ ከትራንስፎረመር ጋር በመጣመር ራቅ እሳካለ ስፍራ ድረስ የኤሌክትሪክ ኀይልን ማስተላለፍ እንደሚቻል እናም አምርቶ የሚገኘው ውጤትም የተሸለ መሆን ተገንዝቦ፤ በ1887 የዌስቲነግስተኑ ኤሌክትሪክ ድርጅትተመሰረተ በዚህም ዊሊያም ስታንሌይ.የተባለውን መሀንዲስ በመቅጠር የሀንጋሪያኖቹን (ዜድ ቢዲ የእና ጊብስ) የትራንስፎርመር ዲዛይን በመጠቀም የመጀመሪያውን የሚሰራ ትራንስፎርመር ጥቅም ላይ መዋል ቻሉ፡፡ በ1887 መጨረሻ ዌስቲንግስተን 68 የኤሲ ጣቢያዎች ሲኖሩት፤ኤዲሶን 121 ዲሲ ጣቢያዎች ነበሩት፤ ይህም በዚህ እንዳለ እንደ ኤዲሰን ተፎካካሮዎች መብዛታቸው ሁሉ የፓተንት ችግርንም በመሸሽ የየራሳቸውን ዲዛይን በመጠቀም፤ ለምሳሌም የሳውየር ማን ኢንካነዴሰንት አምፖል ዲዛይን ለዌስቲንግሀውስ በመተው ፤ ስለዚህም ሌላኛው ድረጅት ተሆምሰን ሆውስተን ኤሌክትሪክ ድርጅት ከፍተኛ ቮልቴጅ ኤሲ ሴፍቲ ጌዳይ በማሰብ የመብረቅ ተከላላይ ለማስተላለፊያ መስመሩ እንዲሁም የማግነቲክ ስዊች ለኃይል መዛባት ተቆጣጣሪ ሰሩ ይሄን ሲሰተሞች ዌስቲንግስተኑ ድርጅት የለውም ነበር፡፡ ተያያዥ ጉዳዮች በኒውዮርክ ከተማ በፖል እንጨት ላይ በተንጠለጠሉት የቴሌግራፍ፤ የስልክ፤ የእሳት አደጋ ተቆጣጣሪ እና አመልካች ገመዶች ከከፍተኛ ኤሌክትሪክ ሀይል ገመዶች ጋር ተደምሮ ለአይን ብዥ ያለ ምስል ከመፍጠሩ በተጨማሪ በ1888 በረዶ ክምር ጊዜ መስመሮች በመቆራረጣቸው ደንበኞች ቅሬታ አስነስቶም ነበር፤ ኮንዳክተሩ መሸፈኛ ኢንሱሌተር ወይንም ኤልክትሪክ የማያስተላልፍ ፐላስቲክ ከሞላ ጎደል ነበር ስለዚህም ለብዙ ሰዎች ህልፈተ ህይወት አስከተለ፤ የ15 አመት እድሜ ልጅ የተቆረጠ የቱሌግራፍ መስመር ከኤልክትሪክ ገመድ ጋር በመነካካቱ፤ ጆን ፊክ የሚባል ዌስተርን ዩኒየን የመስመር ሰራተኛ ከመሬት በላይ በጠንጠለጠለ ሽቦ የዝቅተኛ ቮልቴጅ የቴሌግራፍ መስመር ሲጠግን ሳይወቀው ከከፈተኛ ኤሌክትሪከ መስመር ጋር በመነካካቱ ወዲያወኑ ሲሞት ለረጀም ጊዜ በሾክ ሰውነቱ ሲርገፈገፍ በሚጨናነቀው የማንሃተን ጎዳና ላይ ብዙ ሰው እያየው ነበር፡፡ በዚህም ወቅት የኒውዮርክ የመገናኛ በዝኋን ወሬቸውን ከኤልክትሪክ ብረሃን ወይስ ብርሀን በጋዝ(የቀድሞውን) ወደ ሞት በሽቦ የሚል አርእስት ቀይረውት ነበር፡፡ እናም የኤሲ አምራች እና አከፋፋይ ድርጅቶች በህግ እንዲጠየቁ ጠይቀው ነበር፡፡ በዚህም ጊዜ ኤዲሰን ለመጀመሪያ ጊዜ በግልፅ ኤሲ ሲስተምን ኮነነ ፤ ይሁን እና ዌስቲንግ ይህን ሙከራ ተቀውሞ ኤሲ ለማጣጣል የተደረገ ነው ሲል ይህንንም የሚያሰሩት እነ ኤዲሰን ናቸው ሲል ቅሬታውን አሰማ፡፡ የኒው ኦርሊንስ ታይምስ () እንዲህ ብሎ ዘግቦ ነበር፤ (ሞት ከበራፍ ላይ አይቆምም ነገር ግን ወደ ውስጥ ይገባል ምንአልባትም በሩን ዘግታችሁ መብራቱን ወይንም ጋዙን ስተለኩሱት ሊወስዳችሁ ይችላል) ለድንገተኛ ሞት የሚያጋልጥ የኤልክትሪክ አደጋ በዚህ ወቅት አዲስ ነገር ነበር፣ መከላከያ ያልለበሱ የመስመር ሰራተኞች ለዚህም ዋንኞች ተጋላጮች ነበሩ፤ ለዚህም የጥርስ ሀኪሙ አልፍሬድ ይሄንን ክስተት ለመቆጣጠር ሲሰራ በውሾች ላይ ሙከራ በማድረግ ብዙ ውሾችን ከገደለ በሆላ እንደውም የኤሲ ዘዴ ከስቅላት ፍርድ እነደ ተለዋጭ እንደሚያገለግል ታውቆ የኤሌክትሪክ ወንበር በኒው ዮርክ ፖሊሶች ጥሩ ስቃይ የሌለበት ሆኖ ተገኘ፤ እናም በ1889 ኒውዮርክ የመጀመሪያውን የሞት ፍርድ በኤሌክትሪክ ወንበር ዊሊያም ኬምለር በተባለ ወንጀለኛ ላይ ሞከሩ፡፡ በሌላም በኩል ሃሮልድ ብራውን የተባለ ኤሌክትሪክ መሀንዲስ ለኒውዮርክ ፖስት በፃፋው ደብዳቤው የችግሩ መንስኤ ይህ ተለዋዋጭ ሀይል መጠቀም መጀመሩ እናም አደገኛ ከመሆኑ አንፃር ህብረተሰቡን ለቀጥተኛ ሆነ የአደጋ ሁኔታ ውስጥ እንደከተተው እና የኃይል መጠኑን ከ300 ቮልት በታች ማድረግ እንደሚገባ በዚም በወቅቱ የነበሩት ባለሙያዎች የኤሲ እና የዲሲ ልዩነቶችን በማጤን እውቀታቸውን የፈተኑበት ሆኖም ልክ እንደ ኤሲውም ሁሉ ዲሲው ምንም እንኮን የሞት አደጋ ባያስከትልም በተለያዩ ቦታዎች ለእሳት አደጋ መከሰት መንስኤ እንደሆኑ ያስረዱበት ወቅት ነበር፡፡ የሳይንስ ሙከራ ይጎልሃል የተባለው ኤንጂነር ሀርሎድም ከኤዲሰነ ጋር በመወያየት በኮሎምቢያ ኮሌጅ ለተሳታፊዎች በዉሾች ላይ በደረገው ሙከራ፤ በመጀመሪያ አንድን ውሻ እስከ 100ቮ ዲሲ ሾክ ቢያደርገውም ምንም አልሆነም ቀጥሎም በ300ቮ ኤሲ ሌሎች ውሾች ወዲያው ሲሞቱ በማሳየት የኤሲን አደገኝነት አሳይቶ የነበረ ቢሆንም ግን ኤሲ እያሳየ ካለው እድገት አንፃር ውሳኔ ሊወሰደበት አልቻለም ነበር፡፡ ይህ የከረንቶች አጠቃቀም ፍልሚያ ቶማስ ኤዲሰን እና ጆርጅ ዌስቲነገሀውስ ወደ ክስረት እየከተታቸው ሄደ፡፡ በዚህ ወቅት ዌስቲነገሀውስ ኃይሉን እና አቅሙን በመስፋፋት ሌሎች ድርጅቶችን በመግዛት የሳውየር ማን የአምፖል ፓተንት በመጠቅለል የኢንደክሽን ሜትር የሚሽከረከር ማግኔቲክ ፊልድ የሚጠቀም በድርጅቱ ውስጥ በማሰራት የኤልክትሪክ ክፍያውን መቆጣጠር ችሎም፤ ኒኮላስ ቴስላን የተባለው ቀድም ብሎ ለኤዲሰን ለመስራት ከ አውሮፓ፤ ቡዳፔስት፤ የመጣ ቀጥሎም በኤዲሰን ዲሲ ሲሰተም ባለመስማማቱ በግሉ መስራት ጀምሮ ቀጥሎም የፖሊፌዝ ኢንደክሽን ሞተር ፓተንትም በማግኘቱ ከዌስቲንግ ጋር በመስራቱ፤ የጋሊሊኦ ፌራሪስንም ጨምሮ ከሌሎች የፓተንት ችግሮችም በማቃለል ዌስቲነገሀውስ ድርጅቱን ወደ ተደራጀ ኤሲ ሲሰተም አስገባ፡፡ ኤዲሰን በበኩሉ የኤዲሰን ላመፕ ካምፓኒ፣ ኤዲሰን ማሽን ዎረክስ የዳይናሞ እና የኤሌክትሪክ ሞተሮች ፋብሪካ ፤ በርግማን ናድርጅቱ የሶኬቶች እና ሌሎች የእሌክትሪክ መብራት እቃዎች እና የባሀብቶችንም እገዛ እንደ ጄ.ፒ. ሞረጋን እና የቫነደርቢለት ፋሚሊ እና ሄነሪ ቪላርድ እሱም በበኩሉ ድርጅቱን ለማጠናከር ሞኩሮ ድርጅቱም አሁን ኤዲሰን ጄኔራል ኤሌክትሪክ ተብሎ ተሰየመ፡፡ ቀጥሎም ከአምስት አመት በፊት 15 የሚደረሱት የኤልክትሪክ ኩባኝያ ድርጅቶች አሁን ወደ ጄኔራል ኤሌክትሪክ እና ዌስቲነገሀውስ በፋይናንሽያል እጥረት እንዲሁም ኤዲሰን በዲሲተመራጭነት በማጣታቸው አንድ ሆነው መስራት ጀመሩ ይሁን እና ኤዲሶን ድርጅቱ እና የመበት ፍቃዶቹ የሱ ስለነበሩ ቅሬታ ፈጥረውበት ነበር፡፡ በ1892 ዌስቲነግ በዎርልድስ ኮሎምቢያን ኤግዚቢሽን የኤሲ ሲስተም ለብዙ እቃዎች ሐይል ሲሰጥ በማሳየቱ በኒያግራ ፎልስ ላይለሚሰራው የመጀመሪያ የኤሲ ሀይል ማመንጫ ጣቢያ ኮንትረክት አሸነፈ በዚህም የ ኤዲሰን ድርጅት ተቀጣሪ ቻርልስ ፐ. ስቴይንመየትዝ የኤሲ ኔትዎረክ የሂሳብ ማረጋገጫን በማገኘቱ ጄኔራል ኤሌክትሪክም የጨረታው ተካፋይ መሆን ችሎ ነበር በዚህም የዲዛይኖች መሻሻል በአዳዲስ ተቀጣሪ መሀንዲሶች ለትራንስፎርመሮች፤ ለጄኔሬተሮች፤ ለሞተሮች ተገኝቶ ነበር፡፡ እነደዚህም ሆኖ በ1890 ኤዲሰነ ወደ ሌላ ንግድ () ለመግባት አሰበ ፤ እዲሱ ድርጅትም አሁን በኤዲሰን ሙሉ ቁጥጥር ስር ያልሆነው ኤሲ እቃዎችን ማምረት ጀመረኤዲሰን አሁን በድርጅቱ ውስጥ ለሚያሰራው ኤሲ ትራንስፎርመር ፈልሳፊ ለሆነው ዊሊያም ስታንሊ ልጅ ለጆርጅ በ1908 ምንአልባትም የኤሲ እድገት እና ውጤትም ተገንዝቦ እንዲህ ብሎት ነበር(እኔ ስህተተኛ ነበረኩ ብለህ ለአባትህ ንገረው ብሎት ነበር) ፡፡ ነገር ግን ይህ የፋይናንሺያል ድብልቅ በቴክኒክ በኩል ብዙ ይቀረው ነበር ፤ ያሉትን ሁሉ ሀይል ፈላጊእንደ ፋብሪካ ውስ ጥ ያሉ ዲሲ ሞቶሮች፤ ረጅም ርቀት የሚሄዱ የሀይል መስመሮች ፤ የመኪና ባትሪዎች፤ የከፍተኛ ቮለቴጅ አርክ መበራቶች ፣ ፖሊ ፌዝ ኤሲ ኔትዎርኮች፤ ጋር ተቀናጅቶ መስጠት እስፈልጎም ፤ በአውሮፓ እና በአሜሪካ በተገኘየ አዳዲስ ግኝቶች ኤንጂነርድ ዩኒቨርሳል ሲስተም ለመ ጠቀም በዚህም የሞቶር-ጄኔሬተር ጥምረቶችን መጠቀም እናም ሮታሬ ኮንቨርተር የተባሉ ሲሰተሞች ያለው ሲሰተም ከአዲሱ ጋር ማያያዝ አስፈልጎል፡፡ የዕድገት አካሄድ ለምሳሌ - በ1880 በቡረሽ የኤሌክትሪክ ካምፓኒ የ3.2 ኪ.ሜ. የመንገድ መብራት በ3500ቮ. የአርክ ብረሀን ለኒው ዮርክ ከተማ ለምሳሌ ተሰራ፡፡ -በ1882 ኤዲሰነ የመጀመሪያውን የፐርል ስትሪት የኤልክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን በማንሀተን በ110ቮ. ለ59 ደምበኞች አቀረበ፡፡ በማሳቹሴትስ የኤሲ ሲስተም በመጠቀም ከ 500ቮ ወደ 100ቮ በመቀየር ለ23 ደምበኞች እስከ 4 ከ.ሜ. ርቀት ላሉ አቀረበ፡፡ በፍራንክፈረት ጀርመን የረዥም ርቀት 175 ኪ.ሜ የኤሲ ከረንት ኃይል ሲሰጥ ተአይንት ቀረበ፡፡ በ1889 የረዥም ርቀት ዲሲ ማስተላለፊያ በ ኦሬጎን ከተማ ተከፈተ፡ በኒያግራ ፎልስ በ1893 የተጀመረው ዋናው የኤሲ ሲስተም በ25 ሀርትዝ ፍሪኩዌንሲ ነበር ወደ 60 ሀርትዝም በ1950 ነበር የተቀየረው፣ በዚህም ወቅት ቴስላ ኃይል ማመንጫውም ክፍተኛ የኤሲ ኃይል እንዳላውም አረጋግጦም ነበር፡፡ ይህም እድገት እንደዚህ እያለ ቀጥሎ ለምሳሌ የአውሮፓዋ ሄልሰንኪ የዲሲ መስመር እሰከ 1940 ድረስ ነበራት፤ እነ ቦስተን እና ማሳቹሴትስ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የ ዲሲ 110ቮ ተጠቃሚ ነበሩ፤ ሆቴል ኒወ-ዮርከሮቹ እስከ 1960 ድረስ የዲሲ መስመር ተጠቃሚ ነበር፡፡ እናም በአሁኑ ወቅት የኤሲ ከረንት ለኤሌክትሪክ ኃይል የብርሀን አገልግሎት በስፋት ለመዋል ችሏል፡፡
52840
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B5%E1%8D%93%E1%8B%AD%E1%88%A9%E1%88%8A%E1%8A%93
ስፓይሩሊና
የስፓይሩሊና ምንነትና ጥቅሞች ስፓይሩሊና ምንድነው? ስፓይሩሊና የሚለው ስም የተወሰደው ከላቲን ቃል ሲሆን ትርጓሜውም ቀጭን ጥምዝምዝ ማለት ነው፡፡ ስፓይሩሊና በዋነኛነት ከሁለት የሲያኖባክቴሪያ ዓይነቴዎች ማለትም ከአርትሮስፒራ ፕላተንሲስና አርትሮስፒራ ማክሲማ የሚዘጋጁ የሰው ምግብና የእንስሳት ተጨማሪ ምግቦች የሚታወቁበት ስም ነው፡፡ ሌሎች የአርትሮስፒራ ዓይነቴዎች በስፓይሩሊና ዝርያ ስር ተመድበው እንደነበር ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተደረገ ስምምነት ሁለቱም (ስፓይሩሊናና አርትሮስፒራ) ልዩነት ያላቸው ዝርያዎች በመሆናቸው፣ ለምግብነት ጥቅም ላይ የሚውሉት ዓይነቴዎች በአርትሮስፒራ ስር እንዲጠቃለሉ ሆነዋል፡፡ ይሁን እንጂ ትክክለኛም ባይሆን ስፓይሩሊና የሚለው ስም ይበልጥ ታዋቂነት አለው፡፡ አርትሮስፒራ ስፓይሩሊና በመባል ለምግብነት በገበያ የዋሉ የሲያኖባክቴሪያ ዝርያዎችን ይይዛል ማለት ነው፡፡ አርትሮስፒራ ግራም ኔጌቲቭ፣ ሰማያዊ-አረንጓዴ፣ የፀሀይ ብርሃንንና ካርቦንዳይኦክሳይድን እንዲሁም ከኢ-ኢርጋኒክ ውህዶች ኤሌክትሮንን የሚጠቀሙ፣ ቀጫጭን፣ እንድና ከአንድ በላይ የተያያዙ ህዋሳት ያሏቸው፤ በብዙ ወይም በጥቂቱ ጥምዝ የሆኑ የሲያኖባክቴሪያ ዝርያ ናቸው፡፡ የተለያየ የርዝመት መጠን (ከ100-200 ማይክሮን) እና ከ8-10 ማይክሮን የሚደርስ ስፋት አላቸው፡፡ አርትሮስፒራን ከሌሎች ሲያኖባክቴሪያ የተለየ የሚያደርገው የሚኖርበት ስርዓተ ምህዳር ሲሆ ይኸውም ደቂቅ አካሉ በጣም ማእድን በበዛበት፣ ጨዋማና ሞቃት ውሃ መባዛቱ/ማደጉ ነው፡፡ ሌሎች ህይወት ያላቸው አካላት በዚህ አይነቱ ስርዓተ ምህዳር ለመኖር ይከብዳቸዋል፡፡ በዚህ ስርዓተ ምህዳር የሚኖረው አርትሮስፒራ ሌሎችን የሚያስወግድበት መንገድ፡ አርትሮስፒራ የሚኖርበት ስፍራ ያለውን ሶዳ ጨው(ካርቦኔትና ባይካርቦኔት) በመመገብ የውሃውን ጨዋማነት ከፍ ስለሚያደርግ (እስከ 12.5 ፒኤች ስለሚያደርሰው) የአርትሮስፒራ ጥምዝምዞች ደማቅ ቀለማማና በአብዛኛው በውሃ ላይ የሚንሳፈፉ በመኖናቸውና በብቃት የፀሀይ ብርሃንን ስሚከላከሉ፣ ሌሎች ዋቅላሚዎች እንዳይኖሩ ያደርጋሉ፡፡ መቼ ታወቀ? በመጀመሪያ የታወቀው በ1940 (እኤአ) ዴንጊርድ በተባለ ፈረንሳዊ ፋይኮሎጂስት ሲሆን ለጥናቱ መነሻ የሆነውን ናሙና ያገኘው ክሪች ከተባለና በመካከለኛው አፍሪካ በዛሬዋ ቻድ አጠገብ በነበረ በፈረንሳይ ሰራዊት ውስጥ በፋርማሲስትነት ከሚሰራ ጓደኛው ነበር፡፡ ክሪች በአካባቢው የገበያ ስፍራ በትናንሽ ብሽኩጽ መልክ የሚሸጠውን ደረቅ የባክቴሪያ ጥፍጥፍ አግኝቶ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ በኋላ ስለአርትሮስፒራ ፕላተንሲስ ሳይታወቅ 25 ዓመታት ያለፈ ሲሆን እንደገናም ወደ እውቅና የመጣው ጄ.ሌዎናርድ በተባለው ቤልጄማዊ ቦታኒስት ነው፡፡ ለእውቅና መነሻ የሆነውም በቻድ ሀይቅ አካባባ ያሉት ካኔምቡዎች በየመንደሩ ባሉ የሜዳ ላይ ገበያዎች ሰማያዊ-አረንጓዴ ከኬኮችን ለሽያጭ ማቅረባቸው ነበር፡፡ የት ይገኛል? አርትሮስፒራ ፐላተንሲስ የተበለው ዓይነቴ በአፍሪካ፣ በእስያ በደቡብ አሜሪካ የሚገኝ ሲሆ አርትሮስፒራ ማክሲማ ደግሞ በመካከለኛው አሜሪካ ይገኛል፡፡ አርትሮስፒራ ፕላተንሲስ ጥልቅ ባልሆ ጨዋማ ጉድጓዶችና በሶዳ ሃይቆች የፒኤች መጠኑ ከ9-11 በሚደርስና 38.3 ግራም በሊት በሆነ በጣም ከፍተኛ ጨውነት ባለው፣ አብዛኞቹ አካላት ሲኖሩ በማይችሉበት ቦታ ተደላድሎ ይኖራል፡፡ የእሳተገሞራ አፈር አካል የሆኑት ሶድየም ካርቦኔትና ባይካርቦኔት የተባሉት ዋነኛዎቹ የጨዋማነት ማዕድኖች ናቸው፡፡ ከብርሃናዊ አስተፃምሮ አንፃር ደግሞ አርትሮስፒራ ፕላተንሲስ በሚያስደንቅ ሁኔታ ከፍተኛ የኦክሲጅን መጠን አምራች በመሆን ይታወቃል፡፡ የሰው ልጅ ሰውነት የሚፈልገውን ሁሉ በተሟላ ሁኔታ ሊሰጥ የሚችል አንድም ፍራፍሬ፣ ቅጠላቅጠል ወይም የስጋ አይነት የለም፡፡ ስፓይሩሊና ግን ይህን ያሟላል፡፡ ስፓይሩሊና እስከአሁን ከታወቁት ምግቦች ይልቅ እጅግ የበለፀገ ነው፡፡ ስፓይሩሊና በ9ኛው ክፍለ ዘመን በቻድ በነበረው የካኔምብ ግዛት እንኳን ይታወቅ ነበር፡፡ ዛሬም ድረስ የደረቀና በኬክ መልክ የተዘጋጀ አልፎም በሽያጭ የሚቀርበውን “ዲሄ” የሚባለውን በየቀኑ ለምግብነት ይጠቀማሉ፡፡ ዲሄ በትናንሽ ሃይቆ ወይም ጉድጓዶች ላይ የሚንሳፈፍን የአርትሮስፒራ ፕላተንሲስ ግግር በመልምና በማድረቅ ተቆራርጦም ለሽያጭ ይቀርባል፡፡ በተመሳሳይ በ16ኛው ክፍለዘመን በሜክሲኮ ይኖሩ የነበሩ አዚቴክሶች ከቴኮኮ ሃይቅ በመልቀም ስፓይሩሊናን ለምግብነት ይጠቀሙት እንደነበር ይነገራል፡፡ ዛሬ በሚሊዮን የሚቆጠር የዓለም ህዝብ ስፓይሩሊናን ይመገባል፡፡ የሰው ልጅ ሰውነት ለመኖር ከሚያስፈልጉት ንፁህ አየርና ውሃ ባሻገር አስፈላጊ የሆኑ የንጥረ ምግብ ዓይነቶች ይፈልጋል፡፡ እነዚህ ሁሉ ደግሞ በተሟላ ሁኔታ በስፓይሩሊና ውስጥ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ የንጥረ ምግብ ዓይነቶች ገንቢ/ጠጋኝ፣ ሀይልና ሙቀት ሰጪ፣ ቫይታሚን መዕድናት፣ ኤንዛይምና የሰውነት ቀለም ንጥሮች ናቸው፡፡ ስፓይሩሊና ያለውን የጤና ጥቅም ስናይ በቫይረስ አማካኝነት የሚመጡ በሽታዎችን፣ ካንሰርን፣ በደቂቅ አካላት አማካኝነት የሚመጡ በሽታዎችንና ሌሎች በሽታዎችን ለመከላከል ይጠቅማል፡፡ ከነዚህም ባሻገር በደም ውስጥ ያለ የስብ መጠንን፣ የስኳር በሽታን፣ የአይን፣ የደምግፊት በሽታን ለመቆጣጠርና የሰውነት ክብደትን ለመቀነስ እንዲሁም ቁስልን ለማዳን ይጠቅማል፡፡ እንዴት ጥቅም ላይ ይውላል? ስፓይሩሊና በዱቄት፣ በእንክብል፣ በኬክ፣ በብስኩትና በጁስ መልክ እየተዘጋጀ ለሰው ልጅ በዋነ ምግብነትና በተጨማሪ ምግብነት ጥቅም ላይ የሚውል ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር ለአሳ፣ ለዶሮና ለሌሎች በተጨማሪ ምግብነት ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ የስፓይሩሊና ምርት ውዳቂም ተመራጭ የሆነውን ባዮፕላስቲክ ለማምረት ይውላል፡፡
11738
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8A%AD%E1%88%8A%E1%88%89%20%E1%88%80%E1%89%A5%E1%89%B0-%E1%8B%88%E1%88%8D%E1%8B%B5
አክሊሉ ሀብተ-ወልድ
ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሰው ሲሆኑ በ ጣልያን ወረራ ጊዜ አምስቱን ዓመት ሙሉ በፓሪስ የኢትዮጵያ ጉዳይ ፈጻሚ፤ በዠኔቭ በዓለም መንግሥታት ማኅበር የኢትዮጵያ ዋና ጸሐፊ ከድል በኋላም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት እና እስከ አብዮት ፍንዳታ ድረስም በዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስቴር ነበሩ። ከአብዮቱ ፍንዳታ በኋላ አቃቂ ታስረው ከቆዩ በኋላ ያለፍርድ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ከስልሳ ሰዎች ጋር በደርግ ተረሽነው ሞቱ። የተማሪነት ዘመናት አክሊሉ መጋቢት ፭ ቀን ፲፱፻፬ ዓ/ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ቡልጋ ከተወለዱት አለቃ ሀብተወልድ ካብትነህ እና ከወይዘሮ ያደግድጉ ፍልፈሉ ተወልደው የአማርኛ ትምህርታቸውን አዲስ አበባ በሚገኘው የራጉኤል ቤተ ክርስቲያን አጠናቀቁ። ከዚያም በዳግማዊ ምኒልክ ትምሕርት ቤት ለሦስት ዓመታት ዘመናዊ ትምሕርት ከተከታተሉ በኋላ በ፲፱፻፲፯ ዓ/ም ወደ እስክንድርያ ትምሕርታቸውን እዚያ በሚገኘው የፈረንሳይ “ሊሴ” ትምህርት ቤት እንዲቀጥሉ በአልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ መኮንን ተላኩ። እስክንድርያም እስከ ፲፱፻፳፫ ዓ/ም ከተማሩ በኋላ የሊሴ ትምሕርታቸውን አጠናቀው ለከፍተኛ ትምሕርት ወደ ፓሪስ እና ታዋቂው ሶርቦን ዩኒቨርሲቲ አምርተው የከፍተኛ የንግድ ሕግ እና ሽከታኪን () ትምሕርት ጀመሩ። ሶርቦን እስከ ፲፱፻፳፰ ዓ/ም ድረስ ተምረው የመጀመሪያ ሲማክቶ ጉላፕ በሸከታኪን እንዲሁም የ ሲማሕግ ጉላፕ () ተመርቀው ወጡ። ወዲያው ፋሽሽት ኢጣልያ ሀገራችንን ይወርና ወጣቱ አክሊሉ ሀብተወልድ ለውድ አገራቸው ነጻነት የአርበኝነት ትግላቸውን በቶፍካ () እና በገቢ ሰብሳቢነት እዚያው ፈረንሳይ አገር ተሰማሩ። በዓለም መንግሥታት ማኅበር የኢትዮጵያ ዋና ፀሐፊ በጦርነቱ ዋዜማ ኢትዮጵያ በዓለም መንግሥታት ማኅበር ሸንጎ ጣልያን በግፍ ልትወራት መነሳቷን እና በማኅበሩ ‘የጋራ ደህንነት’ ዋስትና () መሠረት አባላት አገሮች መሃል ገብተው ጣልያንን እንዲያስታግሱ በምትከረከርበት ጊዜ አክሊሉ በፈረንሳይ አገር ውስጥ ተማሪ ሆነው ሳሉ ለሀገራቸው የሚያደርጉትን ትግል በመመልከት ንጉሠ ነገሥቱ፤ በዠኔቭ የኢትዮጵያ ልዑካን መሪ ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም ሥር ዋና ፀሐፊ አደረጓቸው። ፊታውራሪው ያንጊዜ በፈረንሳይ፣ በብሪታንያ እና በዠኔቭ የኢትዮጵያ ዋና ልዑክ ነበሩ። ጦርነቱ በይፋ ከመጀመሩ በፊት ወደዠኔቭ እየሄዱ በኢትዮጵያ ስም ከጣልያን ጋር በዓለም መንግሥታት ማኅበር ሸንጎ ይሟገቱ የነበሩት እነዚህ ሁለቱ ስዎች ነበሩ። ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ወደአገራቸው ሲመለሱና ብላቴንጌታ ወልደ ማርያም በፓሪስ የኢትዮጵያ አምባሳዶር ሲሆኑ አክሊሉ የ”ፕሬስ አታሼ” ሆነው እንዲሠሩ ንጉሠ ነገሥቱ ቢያዟቸውም አምባሳደሩ “እምቢ ብለው አላስገባም አሉኝ። ቢሆንም እውጭ ሆቴል ቁጭ ብዬ እንደፕሬስ አታሼ ሆኜ ሥሠራ ነበር።” ( መስከረም ፲ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ለደርግ የምርመራ ኮሚሽን ‘ዓለም በቃኝ’ እስር ቤት ሆነው በላኩት የታሪክ ማስተወሻተው) የሚሉን አክሊሉ ሀብተወልድ በዚሁ ሥራ አፈ ቀላጤ () ሆነው ለጋዜጠኞች ማብራሪያ እና ቃለ ምልልስ በመስጠት የኢትዮጵያን አቋም እና የተሰነዘረባትን ግፈኛ ድርጊት ማስተዋወቃቸውን ቀጠሉ። ለመሆኑ ብላቴንጌታ ወልደ ማርያም ለምን ይሆን አክሊሉን አላስገባም ያሉት። ምናልባት ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ - ሁለተኛ መጽሐፍ” በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “በፓሪስ የኛ ሚኒስቴር የነበረው ብላቴንጌታ ወልደማርያም አየለ እኛን ከድቶ ለጣልያኖች በገባ ጊዜ በዓለም መንግሥታት ማኅበር የኢትዮጵያ ጸሐፊ አቶ አክሊሉ ሀብተወልድ በፓሪስ የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ጉዳይ አስፈጻሚ ሆኖ አገልግሎናል።” ብለው ያሠፈሩት ምክንያቱን ይጠቁም ይሆናል። በወቅቱ የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበረው ፒዬር ላቫል እና የብሪታንያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሳሙኤል ሆር በ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፳፯ ዓ/ም በምስጢር ዶልተው አዘጋጅተውት የነበረውን፤ ኢትዮጵያን የሚበልጠውን አገር (ሐረርን፣ ሲዳሞን፣ ባሌን) ለጣልያን ሰጥታ ጎጃምን፣ ጎንደርን እና ትግሬን አስቀርታ ተጣልያን ጋር እንድትታረቅ የሚደነግገውን የ”ሆር-ላቫል” ስምምነት የሚባለውን ለጃንሆይ መስጠታቸው ሲሰማ አክሊሉ ሀብተወልድ ማዳም ታቡዴስ ለምትባለው የ”ራዲካል ፓርቲ” ጋዜጣ ኃላፊ ለነበረችው ታዋቂ ጋዜጠኛ በምስጢር ይገልጹላትና እሷ ሎንዶን ላይ በጋዜጣና በራዲዮ ይፋ አደረገችው። ጉዳዩ በብሪታንያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትልቅ ውዝግብና ሙግት ተደርጎበት ሆርም ምክር ቤቱን ይቅርታ እንዲጠይቅና ስምምነቱም እንዲወድቅ አድርጎታል። የጠላት ዘመን በሚያዝያ ወር ፲፱፻፳፰ ዓ/ም መደምደሚያ የፈረንሳይ የሕግ አውጪዎች ምክር ቤት አባላት ምርጫ በሚካሄድበት ጊዜ ወጣቱ አክሊሉ ለሦስቱ ዋና ፓርቲዎች የወቅቱ የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስቴር የነበሩት ፒዬር ላቫል ሙሶሊኒን ለማስደሰት ሲል ኢትዮጵያን በመሸጥ “የጋራ ደህንነት” () የተባለውን የዓለም ጸጥታው ምክር ቤትን ዓላማ ማድከሙን፤ የኢትዮጵያ አቤቱታ እንዳይታይ እያደረገ እንደነ ሙሶሊኒና ሂትለርን እንዳበራታ ፣ በዚህም የዓለም ጦርነትን እንዲፋጠን ማድረጉን በዝርዝር ማስረዳትና ለፓርቲዎቹም የላቫልን መንግሥት ለመገልበጥ መሣሪያ መስጠት ለኢትዮጵያ ታላቅ ጥቅም እንደሚሰጥ በመገንዘብ በነዚህ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብሰባ እየተገኙ የኢትዮጵያን እሮሮ ማሰማት ጀመሩ። የፈረንሳይም ጋዜጦች እነኚህን ስብሰባዎች በሚዘግቡ ጊዜ የአክሊሉ ሀብተወልድን ንግግርም ጨምረው ሲያትሙ ሀገራቸው የደረሰባትን የግፍ ወረራ ለመላው የፈረንሳይ ሕዝብ ሲያስተዋውቁ ቆዩ። አዲስ የተመረጠውን የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስቴር ሊዮን ብሎምን አነጋግረው ፈረንሳይ የሙሶሊኒ ፋሽሽት ኢጣልያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ያላትን ይዞታ መቼም ቢሆን እንደማያውቅ አረጋግጦላቸዋል። ወዲያው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በስደት ወደብሪታንያ ሲመጡ አክሊሉም በዚያው በፓሪስ የኢትዮጵያ ጉዳይ ፈጻሚ ሆነው ሲያገለግሉ ቆዩ። መስከረም ፲ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ለደርግ የምርመራ ኮሚሽን ‘ዓለም በቃኝ’ እስር ቤት ሆነው በላኩት የታሪክ ማስተወሻተው እንደነገሩን፤ “በ፲፱፻፴ ዓ/ም የእንግሊዝ ንጉሥና ንግሥት በግብዣ ለጉብኝት ፓሪስ በመጡ ጊዜ ተሌሎች አምባሳደሮች ጋር እኔም ተጠርቼ ሄጄ ነበር። በፕሮቶኮሉ ደንብ የኢትዮጵያና የጣልያን ጉዳይ ፈጻሚዎች አቀማመጣቸው ጎን ለጎን ስለነበር አጠገቡ በምሆንበት ጊዜያት ጣልያኑ በጣም ሲቆጣ እኔም ኃይለኛ ቃል ስለተናገርኩት ጠቡን ሁሉም ሰምተው የፕሮቶኮሉ ሹም በመካከላችን የሌላ አገር ጉዳይ ፈጻሚ አስቀመጠ።” ይላሉ በወቅቱ ጣልያኖች በኢትዮጵያ ላይ “ኋላቀር፤ ባርያ ሻጭ፤ አውሬዎች…. የኛ ተልዕኮ ኢትዮጵያን ማሰልጠን ነው….” እያሉ ፕሮፓጋዳቸውን ያዛምቱ ስለነበር የፈረንሳይ ሕዝብ ስሜቱን ለኛ ስሞታውን ወደነሱ አዙሮ ነበር። ይሄንን በዘለቄታማና ስኬታማ መንገድ ለመከላከል አክሊሉ (ሀ) ከልዩ ልዩ ጋዜጮች ጋር በመገናኘት እውነቱን በማስረዳት (ለ) ተነ ሙሴ ጃንጉል (በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ሥር የፈረንሳይኛ ጋዜጣ ያቋቋመ) እና ከሌሎች ፈረንሳዮች ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን የሚረዱ ሁለት ኮሚቴዎች ( እና ) በማቋቋምና በነዚህ ኮሚቴዎች በኩል የኢትዮጵያን ጉዳይ በብዙ ሺህ ለሚቆጠሩ ፈረንሳዮች በማሰራጨት የሕዝብ ዕርዳታ ለማስገኘት ችለዋል። (ሐ) በነዚሁ ኮሚቴዎች ዕርዳታና መሥራችነት የኢትዮጵያን አቋምና የጣልያንን ግፍ በየጊዜው የሚያስረዳ “ኑቬል ደ ኤትዮፒ” (የኢትዮጵያ ዜና) የሚባል ጋዜጣ ተመሠርቶ እሳቸውም በየጊዜው በጋዜጣው ይጽፉ ነበር። ከድል በኋላ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሲያከትም የተሸናፊዎቹን የጀርመንን እና የጣልያንን ይዞታ፤ የካሳ ጉዳይ እና በድል ጊዜ ከጣልያን ወደ እንግሊዝ አስተዳደር ተላልፈው የነበሩትን የኤርትራን እና የኦጋዴንን ጉዳይ ለመወሰን በየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መሪነት “የሰላም ጉባዔ” በሚካሄድበት ጊዜ አቶ አክሊሉ ሀብተወልድ መጀመሪያ በፓሪሱ ጉባዔ በታዛቢነት በመጨረሻም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት አዲሱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በተመሠረተበት በሳን ፍራንሲስኮ ከተማ የኢትዮጵያን ልዑካን በመምራት ተሳትፈዋል። አክሊሉ ሀብተወልድን ትልቅ የዲፕሎማሲ ሰው መሆናቸውንና በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረኮች ለኢትዮጵያ ብዙ መታገላቸውን የሚያስመሰክርላቸው ዘመን የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ካከተመበት ጊዜ ጀምሮ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ በኅብረታዊ መንግሥት የመዋሐድ ጉዳይ እስከተፈረመበት ኅዳር ወር ፲፱፻፵፪ ዓ/ም ድረስ የነበረው ዘመን ነው። አክሊሉ በእንግሊዝና በኢጣሊያ ተሸንሽና የነበርቸውን አገራቸውን ረጅም ዓመት የፈጀ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በማድረግ አንድ ያደረጉ ታላቅ ዲፕሎማት እንደነበሩ ስለሳቸው ብዙም የተጻፈ መረጃ ማግኘት ቢያስቸግርም በአምባሳደር ዘውዴ ረታ የተጻፈው ‘የኤርትራ ጉዳይ’ የተባለው መጽሐፍ ስለኚህ ሰው ታላቅ ተጋድሎ በሰፊው ተዘርዝሮ ይገኛል :: አምባሳዶር ዘውዴ የኤርትራን ጉዳይ በተመለከተው በዓለም መድረክ ላይ ይካሄድ ስለነበረው ትግል ሲጽፉ ፤ በዚያን ጊዜ በአካባቢ ቡድን ብዛት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኃይል የነበራቸው የላቲን አሜሪካ አገሮች የጣልያን ወገን በመሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩን አክሊሉ ሀብተወልድን እጅግ በጣም ቢያናድዷቸው የተከተለውን ትንቢታዊ ንግግር ከማኅበሩ መድረክ ላይ አደርጉ፦ «በዚህ አጋጣሚ ለባልደረቦቼ የላቲን አሜሪካ አገሮች ተወካዮች፣ በተለይም ለአርጀንቲናው ልዑክ እጅግ በጣም ከባድ ፋይዳ ስላለው ጉዳይ የማስተላልፈው መልዕክት አለኝ። ዛሬ አገሬ ከግብጽ እና ከላይቤሪያ ጋር ሆና እናንተ ከጣልያን ጋር በማደም የአፍሪቃን ሕዝቦች ለመጨቆን የምትጫወቱትን ሚና በጥንቃቄ እየተመለከትን ነው። በቅርብ ጊዜ ውስጥ ግን እዚህ ያለነው ሦስት አፍሪቃውያን አገሮች በአስር እጥፍ በዝተን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ ተገቢ መቀመጫችንን እንይዛለን። ያን ጊዜ እኛ እንደናንተ ሳይሆን፣ ለዓለም ሰላም ድጋፍ እና ፍትሐዊ ፍርድ ድምጻችንን እንደምናሰማ ጥርጣሬ የለኝም።» ሲሉ ስሜታዊ ንግግራቸውን አሰምተዋል። እውነትም ይሄንን በተናገሩ በአሥር ዐመታት ውስጥ አፍሪቃውያን አገሮች በማኅበሩ ውስጥ ትልቁ አኅጉራዊ ቡድን ለመሆን በቁ። ረዥሙ የስደት ዘመን ተጠናቀቀ በ፲፱፻፲፯ ዓ/ም መጀመሪያ ለትምሕርት ከአገራቸው፣ ከትምሕርታቸውም በኋላ በጣልያን የግፍ ወረራ ምክንያት አምስቱን ዓመታት አውሮፓ ቆይተው በተቻላቸውና በተሰጣቸውም መመሪያ ስለአገራቸው ሲታገሉ የኖሩት አክሊሉ፤ ከጠላትም ድል መደረግ በኋላ የሳቸው ዲፕሎማሲያዊ የትግል ሥራ እስከሚገባደድ ድረስ በድካም፤ በጭንቀት እና በህመምም ለብዙ ዓመታት በፓሪስ እና ኒው ዮርክ የኖሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከጥቂት የሥራ ጋደኞቻቸው ጋር በ፲፱፻፵፬ ዓ/ም ወደናፈቋት አገራቸው ተመለሱ። የኤርትራን ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስፈጽመው የተመለሱትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአገራቸው ሕዝብ በተለይም ኤርትራውያን በጣም ሞቅ ባለ ሁኔታ ተቀበሏቸው። ቀደም ብሎ ንጉሠ ነገሥቱ፣ እቴጌ መነን፣ ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ፣ አቶ ይልማ ደሬሳ እና የወለጋ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ የነበሩት ደጃዝማች መኮንን ደስታ የደስታ ቴሌግራም ተልኮላቸው ነበር። ሆኖም ንጉሠ ነገሥቱ መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፵፭ ዓ/ም የኤርትራን ከኢትዮጵያ ጋር በኅብረት መንግሥት መዋሐድ አስመልክተው ባደረጉት ንግግር አንዳንድ ኤርትራውያንን በስም ጠርተው ሲያመሰግኑ፤ ለዚህ ውጤት እጅግ ከፍ ያለ ትግል ያካሄዱትንና ታላቅ ዲፕሎማሲያዊ መስዋዕትነትን ላበረከቱት አክሊሉ ሀብተወልድ ግን በሕዝብ ፊት ምስጋና ያለማቅረባቸው ያሳዝናል። በሚያዝያ ወር ፲፱፻፵፯ ዓ/ም የአክሊሉ ዋና ደጋፊ የነበሩት እና እስከዚያ ጊዜ ድረስ በንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ትልቅ ሥልጣን እና በንጉሠ ነገሥቱም ታማኝነትና ተሰሚነት የነበራቸው ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ ፣ ትክክለኛ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከዚህ ቁልፍ ቦታ ተነስተው መጀመሪያ የአሩሲ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ ቀጥሎም የጋሙ ጎፋ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳድሪ ተደርጉ። አምባሳዶር ዘውዴ ረታ በመጽሐፋቸው ስለዚህ ጉዳይ ሲያወሱ፣ የኤርትራ ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሚካሄድበት ጊዜ አክሊሉ ሀብተወልድ የብሪታንያን የኤርትራ አቋም ነቅፈው በመዝለፋቸው የንጉሠ ነገሥቱ የግል ፀሐፊ የነበሩት እና የብሪታንያ ደጋፊ የሚባሉት አቶ ተፈራ ወርቅ (በኋላ ፀሐፊ ትዕዛዝ) ‘የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ አክሊሉ ለብሪታንያ ይቅርታ ይጠይቅ ሲሉ ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ ግን ያደረገው አግባብ ነው ይቅርታ መጠየቅ የለበትም በሚል ጉዳይ ተከራክረዋል ሲሉን የፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ ከሥልጣን መወገድ ምክንያት ዕውን ይሄ ይሆን ወይ? ሊያስብለን ይችላል። ባህሩ ዘውዴ ደግሞ በተባለው መጽሐፉ ላይ የፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ከሥልጣን መወገድ ዋና ምክኛት የነበሩት የግል ምስጢራዊ የስለላ ድር የዳበሩት እና በዚህም የሚያገኙትን መረጃዎች ለንጉሠ ነገሥቱ በማካፈል ይወደዱ የነበሩት የአክሊሉ ታላቅ ወንድም መኮንን ሀብተወልድ ናቸው ይለናል። እንዴት የፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ የመውደቅ ምክንያት እንደሆኑ ባያብራራልንም ምናልባት በዚሁ የምስጢራዊ ስለላ ድራቸው ‘ትልቅ ምስጢር አግኝተውባቸው ይሆን? ለማለት ያበቃናል። ትክክለኛ ምክንያቱ ይህም ይሁን ያ፣ የፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ መወገድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን አቶ አክሊሉን ግን ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር የሚያቀራርበውን በፀሀፊ ትዕዛዝ ማዕረግ የፅህፈት ሚኒስቴርና እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴርነትን አፍርቶላቸዋል። የታኅሣሥ ግርግር በክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ ጄነራል መንግሥቱ ንዋይ እና በታናሽ ወንድማቸው አቶ ገርማሜ ንዋይ የተጸነሰሰውና ታኅሣሥ ፬ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ተጀምሮ ዓርብ ታኅሣሥ ፯ ቀን አሥራ አምስት መኳንንት፣ ሚኒስቴሮች እና የጦር መኮንኖች መረሸን ያከተመው የታኅሣሥ ግርግር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ፣ ለፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ በታላቅ ወንድማቸው አቶ መኮንን ሀብተወልድ መገደል ትልቅ የግል ሀዘን ላይ ቢጥላቸውም፤ በጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስቴርነት የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት ይመሩ የነበሩት የራስ አበበ አረጋይ በአመጸኞቹ እጅ መገደል ለሳቸው የጠላይ ሚኒስቴርነቱን ማዕርግ እና ሥልጣን አስገኝቶላቸዋል። በጠቅላይ ሚኒስቴርነት እና በፅሕፈት ሚኒስቴርነት በጥምር ሲያገለግሉ ዘመናዊውንና ጥንታዊውን ሥልጣናት በጃቸው በማግባት ለንጉሠ ነገሥቱ ቀርበው በተሰሚነት አብዮቱ እስከፈነዳ ድረስ ሠሩ። የአብዮት ፍንዳታ በ፲፱፻፷፭ ዓ/ም የተቀጣጠለው አብዮታዊ ሽብር በተማሪዎች ሰልፍ፣ የወታደሮች እንቅስቃሴ እንዲሁም የዓለምን ዱኛ () ያናጋው የነዳጅ ማዕቀብ ሲለኮሱ የደርግ ሥልጣንም እየጎለመሰ መጣ። ወታደሮቹም መኮንኖችን ብቻ ሳይሆን የ መንግሥት ባለሥልጣናትንም ጭምር የማሠር ስልጣን እንደሚኖራቸው ንጉሠ ነገሥቱን አሳመኑ። በየካቲት ወር ጠቅላይ ሚኒስቴሩ አክሊሉ ሀብተወልድ ከነ ሚኒስቴሮቻቸው ሥልጣናቸውን ለቀቁ። ‘ተንፏቃቂው አብዮት’ ወዲያው ተተክተው የተሾሙትንም አዲስ ጠቅላይ ሚኒስቴር ልጅ እንዳልካቸው መኮንንም ከሥልጣን አውርዶ ከነ አክሊሉ ሀብተወልድ ጋር ከርቸሌ ከከተተ በኋላ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ባለቤቱን እራሳቸውን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ከሥልጣን አወረደ። ፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ከንጉሠ ነገሥቱ አዝማድ እና ቤተሰቦች፤ መሳፍንት እና መኳንንት፤ ባለሥልጣናትና ወታደራዊ መኮንኖች ጋር በእስራት ከቆዩ በኋላ ያለክስም ያለፍርድ በኅዳር ወር ፲፱፻፷፯ ዓ/ም በተወለዱ በ ስድሳ ሦስት ዓመታቸው ከስልሳ ሰዎች ጋር ተረሽነው ሞቱ። የአክሊሉ ሀብተወልድ ጥቅሶች "… "የደረሰው ይድረስ ደካማ ሆኜ መታየት አልፈልግም :: የሀገሬን ጥቅምና መብት የሚነካ መስሎ ከታየኝ መናገሬን አልተውም ::" "…ሀገሬ ኢትዮጵያ በዓለም ሸንጎ ላይ ፍርድ ተነፍጓት ስታዝን የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም።…..ኢትዮጵያ ያለፉት ታሪኮቿ በትክክል እንዳስረዱት፤ለነፃነቷና ለመንቷ፤በኮሎኒያሊስቶች ጣሊአን ጋር በየጊዜዉ ስተዋጋ፤ያሸነፈችዉ ብቻዋን ነዉ። የተጠቃቺዉም ብቻዋን ስለሆነ፤አገሬ መቸዉንም ለሚደርስባት አደጋ ከማንም እርዳታ አገኛለሁ ብላ አትጠብቅም።ዛሬም ሆነ ነፃነቷን ለመጠበቅ፤ታሪኳን ለማስከበር አስፈላጊዉን ዝግጅት ማድረግ ያለባት፤እሷ ራሷ ብቻ ነች።…" “በዚህ አጋጣሚ ለባልደረቦቼ የላቲን አሜሪካ አገሮች ተወካዮች፣ በተለይም ለአርጀንቲናው ልዑክ እጅግ በጣም ከባድ ፋይዳ ስላለው ጉዳይ የማስተላልፈው መልዕክት አለኝ። ዛሬ አገሬ ከግብጽ እና ከላይቤሪያ ጋር ሆና እናንተ ከጣልያን ጋር በማደም የአፍሪቃን ሕዝቦች ለመጨቆን የምትጫወቱትን ሚና በጥንቃቄ እየተመለከትን ነው። በቅርብ ጊዜ ውስጥ ግን እዚህ ያለነው ሦስት አፍሪቃውያን አገሮች በአስር እጥፍ በዝተን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ ተገቢ መቀመጫችንን እንይዛለን። ያን ጊዜ እኛ እንደናንተ ሳይሆን፣ ለዓለም ሰላም ድጋፍ እና ፍትሐዊ ፍርድ ድምጻችንን እንደምናሰማ ጥርጣሬ የለኝም።” ዋቢ ምንጮች ጦብያ መጽሔት ፪ኛ ዓመት ቁጥር ፮ መስከረም ፲፱፻፹፮ ዓ/ም የኢትዮጵያ ካቢኔ አባላት
32861
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8D%E1%8B%B5%E1%89%A5
ግድብ
ግድብ ማለት ከመሬት ስር ያለንም ሆነ ከመሬት ላይ (ሸለቆ ውስጥ) የሚፈስን ውሃ ገድቦ ወይንም አንቆ የሚይዝና ሰው ሰራሽ ሃይቅ ለመፍጠር የሚረዳ እንቅፋት ነው። በጐንና በጐን የሚገኙት ሸለቆዎችም የግድቡ አካል ሲሆኑ የሃይቁን የጎንዮሽ ዳርቻዎችን ይወስናሉ። ግድብ የሚለው ቃል የግድብ አካል የሆኑ የግንባታ ክፍሎችን ማለትም እንቅፋት ፈጣሪውን አካል፣ ውሃ የታቆረበትን አካባቢ፣ ውሃውን ለመጠቀም የሚረዱ ግንባታዎችን እንዲሁም የውሃ መጠንን ለመቆጣጠር የሚረዱ ግንባታዎችን ያጠቃልላል። ግድብን ከውሃ መጠን መቆጣጠሪያ (ዊር) የሚለየው ሙሉ በሙሉ ሸለቆውን እንዲዘጋ ተደርጐ የሚገነባ በመሆኑ ነው። የግድብ አገልግሎቶች ግድቦች ለሚከተሉት አገልግሎቶች ሊውሉ ይችላሉ ለመጠጥ ወይም ለፋብሪካ ግብአት የሚሆን ውሃ ለማከማቸት የሃይል ማመንጫ አገልግሎት (ውሃ ለማጠራቀም እና የከፍታ ልዩነት ለመፍጠር) ለመስኖ ስራ የሚሆን ውሃ ለማከማቸት የጐርፍ አደጋን ለመከላከል የወንዝ ውሃ ከፍታን ለመጨመርና የጀልባ ወይም የመርከብ ጉዞን ለማስቻል ለእስፖርትና ለመዝናኛ አገልግሎት የሚውሉ ሰው ሠራሽ ሃይቆችን ለመፍጠር የማጠራቀም ችሎታ የግድብን የማጠራቀም ችሎታ ግድቡ ማቆር የሚችለውን መጠን በአመት ውስጥ ወደ ግድቡ ለሚፈሰው የውሃ መጠን በማካፈል መመዘን ይቻላል። ጥሩ የማጠራቀም ችሎታ ያላቸው ግድቦች የማጠራቀም ችሎታ 1 ነው። የውሃ መጥለቅለቅ ችግርን ለመቅረፍና የወንዞችን ከፍታ ለመጨመር ለሚሠሩ ግድቦች 0.3 የማጠራቀም ችሎታ በቂ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የግድብ አይነቶች ግድቦች በብዙ መንገድ ተሰርተው ይገኛሉ፣ ለምሳሌ በሰው ልጅ አቅድ፣ ወይንም ደግሞ እንዲሁ በተፈጥሮ ሂደት፣ አልፎ አልፎ ደግሞ በዱር አራዊት፣ ለምሳሌ በድብ ተሰርተው ይገኛሉ። ሰው ሠራሽ ግድቦች በመጠናቸው (በቁመታቸው)፣ በተሠሩበት አላማ እና በአወቃቀራቸው ከፋፍሎ ማየት ይቻላል። ሰው ሠራሽ የግድብ ዓይነቶች ከመዋቅር አንጻር፡ ግስበት ግድብ ግስበት ግድብ ባለው ግዙፍነት ምክንያት የመሬት ስበትን በመጠቀም የውሃን ሃይልና ሌሎች ጫናዎችን ተቋቁሞ የሚቆም የግድብ አይነት ነው። የድልዳሎ ግድቦችና ከብደት ያላቸው የግንብ ግድቦች ዋነኞቹ የግስበት ግድብ አይነቶች ናቸው። ድልዳሎ ግድብ የድልዳሎ ግድቦች ከአፈር እና ከድንጋይ ተደልድለው የሚሠሩ ግድቦች ናቸው። የድልዳሎ ግድቦች በክብደታቸውና ዝቅተኛ ተዳፋትነት ባላቸው ጐኖቻቸው አማካኝነት ሚዛናቸውን ይጠብቃሉ። የድልዳሎ ግድቦች መሀላቸው ወይም በውሃ አቅጣጫ ያለው ውጫዊ አካላቸው ውሃ እንዳያሰርግ ተደርገው ይገነባሉ። ውጫዊ የስርገት መከላከያ ውጫዊ የስርገት መከላከያ በሚጠራቀመው ውሃ አቅጣጫ ከግድቡ የጎን ውጫዊ አካል ላይ ከሸክላ አፈር ወይም ከአስፋልት የሚሰራ የግድቡ አካል ነው። ውጫዊ የስርገት መከላከያ በአየር መፈራረቅና በውሃ ማዕበል ምክንያት ለሚመጡ ጉዳቶች ተጋላጭ ስለሆነ ጥቅም ላይ በሚውልበት ጊዜ እነዚህን ተቃርኖዎች ግምት ውስጥ ማስገባት ያስፈልጋል። ውስጣዊ የስርገት መከላከያ ውስጣዊ የስርገት መከላከያ በግድቡ መሀል በአብዛኛው ከሸክላ አፈር የሚሠራ ሲሆን የግንባታ ስራው ከተጠናቀቀ በኋላ የእድሳት ወይም የማሻሻል ሥራ ለማድረግ በጣም ከባድ ነው። ከዚህም በተጨማሪ የውሃው ግፊት የሚያርፈው በቀጥታ በስርገት መከላከያው ላይ ስለሆነ የውሃ ግፊቱን ለመቋቋም የሚረዳው የግድቡ አካል ከስርገት መከላከያው ጀርባ ያለው የግድቡ ክፍል ብቻ ይሆናል። በዚህም ምክንያት ውጫዊ የስርገት መከላከያ ካላቸው ግድቦች ጋር ሲነፃፀር የውስጣዊ ስርገት መከላከያ ያላቸው ግድቦች መጠን (ግዝፈት) ትልቅ ሲሆን ለግንባታ የሚያስፈልገው ቁስ መጠንም ብዛት ያለው ነው። የግንብ ግድብ የግንብ ግድቦች ከግስበት ግድቦች የሚመደቡ ሲሆን ከኮንክሪት ?? ወይም ከሲሚንቶና አሸዋ ድብልቅ (ሞርታር) በተያያዙ ድንጋዮች የሚሰሩ ናቸው። የግንብ ግድቦች ቅርፅ በአመዛኙ ሶስት ማዕዘናማ አይነት ሲሆን በውሃ በኩል ያለው ጎን ወደ ቀጥታ ያመዘነ ሆኖ ከውሃው በተቃራኒ በኩል ያለው ጐን በአንፃሩ ያጋደለ ነው። የግንብ ግድቦች የታች ስፋት ከቁመታቸው ጋር ሲነፃፀር 2 ለ 3 የሆነ ምጥጥን ሲኖረው ወደ አናታቸው ሲሄድ ስፋታቸው እየቀነሰ ሄዶ አናቱ ላይ ለመኪና መጒጒዋዣ ያህል ሊሆን የሚችል ስፋት አላቸው። ቅስት ግድብ ቅስት ግድብ ከቅስት የሚሰራ ሲሆን የሚያቁረውን ውሃ ሃይል የሚቋቋመው ከቅስቱ ጉልበት የመቋቋም ባህርይ ተነስቶ ነው። ቅስት ግስበት ግድብ ባራጅ ግድብ ብዙ በሮች ያሉት የግድብ አይነት ሲሆን በሮቹን በመክፈትና በመዝጋት በውስጡ የሚያልፍን የውሃ መጠን ለመቆጣጠር የሚያገለግል የግድብ አይነት ነው። ለመስኖ ስራ ያገልግላል። ሰው ሠራሽ የግድብ ዓይነቶች ከጥቅም አንጻር፡ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድቦች 19% የአለምን የኤሌክትሪክ ፍላጎት ያሟላሉ። ታዳሽ ከሚባሉት የኤሌክትሪክ ማመንጫዎች ደግሞ 68% ይይዛሉ።
51363
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%93%E1%88%B5%E1%8B%8B%E1%8A%95
ፓስዋን
ፓስዋኖች ከምስራቅ ህንድ የመጡ “ጌህሎት ራጁት” ማህበረሰብ ናቸው።ዱሳድ ተብሎም የሚታወቀው ፓስዋን ከምስራቅ ህንድ የመጣ የዳሊት ማህበረሰብ ነው ፡ እነሱ የሚገኙት በዋነኝነት በቢሃር ፣ ኡታር ፕራዴሽ እና ጃሀርሃንድ ግዛቶች ውስጥ ነው ፡ የኡርዱ ቃል ፓስዋን ማለት የሰውነት ጠባቂ ወይም “የሚከላከል” ማለት ነው ፡ የቃሉ አመጣጥ በማኅበረሰቡ እምነት መሠረት በብሪታንያ ምስራቅ ህንድ ኩባንያ ትዕዛዝ የቤንጋል ናዋብ ሲራጅ-ኡዱላህ ላይ በተደረገው ውጊያ ላይ ተሳትፎን የሚይዝ ሲሆን ከዚያ በኋላ በሾውዳርስ እና የ ለ የሚይዝበት ቀረጥ ሰብሳቢው . ደፋርነታቸውን ለማረጋገጥ በእሳት ላይ መራመድ ያሉ የተወሰኑ የአምልኮ ሥርዓቶችን ይከተላሉ ፡፡ ሥር-ነክ ጥናት በማኅበራዊ ሁኔታቸው ውስጥ መሻትን ለመፈለግ ፓስዋውያን መገኛቸውን ከብዙ ሰዎች እና ገጸ-ባህሪ ገጸ-ባሕሪያት ይናገራሉ ፡፡ አንዳንዶች እነርሱ የመነጨው ብለው ያምናሉ , ከሰው በላይ እና ውስጥ ፕላኔቶች አንዱ የሂንዱ ሌሎች ያላቸውን ምንጫቸው ይናገራሉ አፈ , ወደ አንዱ አለቃ. "" ከ ምንጭ በተመለከተ የይገባኛል ደግሞ አንዳንድ በማድረግ የማያቋርጥ ነው እነርሱ ግን ጋር ተያይዞ ዘንድ እንደ ምን እንደ ሌሎች የበታች አድርጎ እነዚህ ሰዎች ቢነሱም መመልከት እንዲሁም በአንዳንድ ቡሚሃርስስ በሁለት የተለያዩ ተዋንያን ወንዶች እና ሴቶች መካከል የመስቀል ጋብቻ ዘሮች እንደሆኑ ተከራክሯል ፡፡ ሆኖም የፓስዋን ማህበረሰብ እነዚህን ፅንሰ-ሀሳቦች ውድቅ አድርጎ ‹ዱዳድ› የሚለው ስም መነሻው በዱሳድ ነው የሚል ሲሆን ይህም ትርጉሙ “ለመሸነፍ አስቸጋሪ ነው” ማለት ነው ፡፡ የማይዳሰሱ ማህበረሰብ እንደሆኑ ተደርገው ተቆጥረዋል ፡ በቢሃር ውስጥ እነሱ በዋነኝነት መሬት አልባ ፣ የግብርና ሠራተኞች እና በታሪክ ውስጥ የመንደሩ ጠባቂዎች እና መልእክተኞች ነበሩ ፡ ከ 1900 በፊትም በተለይም በዩታር ፕራዴሽ እና በቢሃር ውስጥ አሳማዎችን ወደ ኋላ ይደግፉ ነበር ፡ ፓስዋንስ ሙስሊሞችን ለመቃወም እንደ ስትራቴጂ በመጥቀስ አሳማዎችን የማሳደግ ሥራ ይከላከላሉ ፡ እነሱ እራሳቸውን ያረጋግጣሉ ፣ የፓስዋን ሴት ልጆች ከሙስሊሞች ለመጠበቅ ሲሉ ከአሳማ አጥንቶች የተሰሩ ክታቦችን ይለብሱ ነበር እንዲሁም አሳማዎችን በአሳማዎች በመጥላት አሳማቸውን በራቸው ላይ ያደርጉ ነበር ፡፡ ጀምሮ መካከል ራጃስታን እንዲሁም የሚፈለግ የዱር አሳማዎች እንደ ይህንን እውነታ እውነታ ቈጠራ በዚህ ስራ ለመከላከል በእነሱ በኩል ደግሞ ጥቅም ላይ ነው ያደገው መሆኑን መጨረሻ በኋላ ሥርዓት, ወደ ከእጅ ማቅረብ አልቻለም ጠባቂዎች ሆነው በማገልገል ያለውን ባህላዊ ወረራ እነሱን የ ከታሪክ የማርሻል በማሳደድ ጋር ተያይዘው ተደርጓል በ ፈንታ ተዋጋ እና ብዙ የምስራቅ ሕንድ ኩባንያ በ ቤንጋል ጦር በ 18 ኛው መቶ ዘመን. የ ህንድ 2011 የሕዝብ ቆጠራ ኡታር ፕራዴሽ ለ ሆኖ ሊመደብ ነው ይህም ህዝብ, አሳየኝ የተያዘለት ካስት 230.593 መሆን እንደ. ይኸው የሕዝብ ቆጠራ በቢሃር ውስጥ 4,945,165 ህዝብ ያሳያል። የ ያለው ባሕላዊ ጀግና ነው . በፓስዋን ባህላዊ ታሪክ ውስጥ የቻውሃርማል እና ረሻማ ተረት የታወቀ ነው ፡፡ , ኃይለኛ ሴት ልጅ ባለንብረቱ, የአባቷን ፍላጎት ላይ ሊያገባት ያባብላል አሉ. በመጨረሻም በእነርሱ ላይ ማህበረሰብ ድል በሚያመለክተው የሚወደው አባትና ሽንፈቶችን እሱን እስኪያጋጥሙን ከጨቋኞች. ወደ ተረት ሌሎች ስሪቶች በአንድ ውስጥ የተወለደው በመናገር ይህን ኃይልን መልእክት ውድቅ ሚስቱ ሆኖ የተወለደው ሳለ ቀደም ልደት ውስጥ ቤተሰብ. ከኩሃርማል ባባ በስተቀር የተወሰኑ ዱሳድ እንዲሁ ጋሪያሪያ ባባን ያመልካሉ ፡፡ ይህ የቃል ጀግና እንደ የቃል ወጎቻቸው በሕንድ ውስጥ የሙጋልን አገዛዝ ዘመናዊ ነው ፡ ወደ መሠረት አንድ ፈረስ ለመንዳት ጥቅም እንዲሁም የራሱን ነገር ግን ደግሞ በሌላ ብቻ የተጠበቁ ሂንዱዎች ደግሞ ጨምሮ ወታደሮች እና በኃይል ውይይቶችን ተቋቁማ ከ እስልምና . ባባ መንደሩ ዳርቻ በሚገኘው ቤቱ ፊት ለፊት የአሳማውን ጭንቅላት ይቀብረው ነበር ፡፡ አሳማዎች ለሙስሊሞች የተፀየፉ በመሆናቸው መንደሩን በብዛት ሙስሊም ከሆኑት የሙጋል ወታደሮች ወረራ ይጠብቀዋል ፡፡ ታደርጋለች ጀመረ በቀዳሚ ግምገማዎች ላይ አንድ በጣም. ስም ብዙ ለውጦች ውስጥ የጥንት ዘመናት እንደ ቤተሰብ ስሞች ነበሩ ስለጀመሩ ቅድሚያ የሚሰጡዋቸውን እነዲሆን በታሪክ. ነበር ማን ስለጀመሩ ቅድሚያ የሚሰጡዋቸውን ስለጀመሩ ቅድሚያ አሁን እና ለአባቱም . ሕዝብ ማህበር ነበሩ የታዘዘ የተለያዩ ስእሎች እንደ ቅር, አርክቴክቸር እና ቤተመቅደስ ህንፃ. በውጤቱም, ሕዝብ ወደ ሌሎች የዓለማችን ክፍሎች እና የኤኮኖሚ ሁኔታ ነው እነዚያ ስለጀመሩ ቅድሚያ አለው የቤተሰብ አባላት በይፋ የሚሰጡዋቸውን በዓሇም ዘሪያ በመላ ታሪክ የሚሰጡዋቸውን የሚሰጡዋቸውን አዲስ ቋንቋ ባህል እና የማህበረሰብ ግብይት ብዙ ተጨማሪ ስለጀመሩ ስም.
15734
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%AB%E1%89%B2%E1%89%B5%20%E1%8D%AB
የካቲት ፫
የካቲት ፫ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፶፫ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፪፻፲፫ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፲፪ ቀናት ይቀራሉ። ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፯፻፰ ዓ/ም - በእስራት ላይ የነበሩት የ ፳፩ ዓመቱ ጎልማሳና የንጉሥ ኢያሱ አድያም ሰገድ ልጅ ዳግማዊ ዓፄ ዳዊት እንደነገሡ አዋጅ ተነገረ። የዘመነ መሳፍንት የመጨረሻው ጦርነት 166ኛ ዓመት መታሰቢያ ደጃዝማች ካሣ ኃይሉ፣ ‹‹ዳግማዊ ቴዎድሮስ ንጉሰ ነገሥት ዘኢትዮጵያ›› ተብለው ከመንገሳቸው በፊት የስሜንና የትግራይ ገዢ ከነበሩት ከደጃዝማች ውቤ ኃይለማርያም (የዳግማዊ ቴዎድሮስ ባለቤት የእቴጌ ጥሩወርቅ ውቤ አባት) ጋር የመጨረሻውን የዘመነ መሳፍንት ጦርነት ያደረጉት ከዛሬ 166 ዓመታት በፊት (የካቲት 3 ቀን 1847 ዓ.ም) ነበር፡ ደጃዝማች ካሣ በኅዳር ወር 1845 ዓ.ም ደጃዝማች ጎሹ ዘውዴን ጉርአምባ ላይ፣ በሰኔ ወር 1845 ዓ.ም ደገሞ ራስ አሊ አሉላን (ዳግማዊ አሊን) አይሻል ላይ ካሸነፉ በኋላ ከወቅቱ የግዛት ኃያላን መሳፍንት መካከል ለደጃዝማች ካሣ ያልገበሩት የስሜንና የትግራይ ገዢ የነበሩት ደጃዝማች ውቤ ኃይለማርያም ብቻ ነበሩ፡፡ ደጃዝማች ካሣም ወደ ደጃዝማች ውቤ ኃይለማርያም ለመዝመት አቀዱ፡፡ ከዘመቻቸው በፊትም ደጃዝማች ውቤ በሰላም እንዲገቡላቸውና እምቢ የሚሉ ከሆነ እምቢታቸው እንደማይበጃቸው የማስጠንቀቂያ መልዕክት ላኩባቸው፡፡ - - - ደጃዝማች ውቤ ኃይለማርያም ከፊትም ጀምሮ ደጃዝማች ማሩ እና ራስ ይማም፤ ደጃዝማች ሰባጋዲስ እና ራስ ማርዬ በሚዋጉበት ጊዜ በብልጠትና በዘዴ አንዱን ከሌላው ጋር እያዋጉ፣ ከሚመቻቸው ጋር እየወገኑና በጋብቻ እየተዛመዱ፤ ሲሸነፉም እየገበሩ ራሳቸውን ከአደጋ ጠብቀው ይኖሩ ነበር፡፡ ደረስጌ ማርያምን አሰርተው ለመንገሥ ጊዜ ሲጠባበቁ የደጃዝማች ካሣ ተደጋጋሚ ድል ዓይኑን አፍጥጦ በላያቸው ላይ መጣባቸው፡፡ ይባስ ብሎም ለደጃዝማች ካሣ እንዲገብሩ የሚያሳስብ መልዕክት ደረሳቸው፡፡ ደጃዝማች ውቤ ኃይለማርያም የደጃዝማች ካሣ መልዕክት ሲደርሳቸው … ‹‹ምን የጠገበ ነው?! ሳልዋጋ ይገባልኛል ብሎ ነው?!›› በማለት ከተናገሩ በኋላ ‹‹አልገባም!›› የሚል ምላሽ ሰጡ፡፡ ጳጳሱ አቡነ ሰላማም ለደጃዝማች ውቤ ‹‹ለካሳ ቢገብሩ ይሻላል›› ቢሏቸውም የስሜኑ ሰው ሃሳባቸውን ሳይቀይሩ ቀሩ፡፡ - - - ደጃዝማች ካሣም ጦራቸውን አስከትተው ‹‹… ከእኔ የተለየህ ለራስህ እወቅ! በምን ጠፋሁ እንዳትል! አይዞህ ወታደር፤ እኔ ደስ ከሚልህ አገር አገባሃለሁ›› የሚል አዋጅ አስነገሩ፡፡ ሕዝቡም ከራስ አሊ መሸነፍ በኋላ ‹‹ደጃች ካሣ መቼ ይነግሱ ይሆን? ስመ መንግሥታቸውስ ማን ይባል ይሆን?›› እያለ ይጠይቅ ስለነበር ‹‹እኔ በመራሁህ ተጓዝ፤ ስሜን በስሜን እነግርሃለሁ›› ብለው ከአምባጫራ አልፈው በወገራ በኩል አድርገው ስሜን ገቡና ደረስጌ ላይ ‹‹እንጨት ካብ›› በተባለ ቦታ ሰፈሩ፡፡ የደጃዝማች ውቤ ጦርም በአካባቢው (‹‹መከሁ›› በተባለች ቦታ) ሰፍሮ ነበር፡፡ ደጃዝማች ካሣም አብሯቸው የነበረውንና ዮሐንስ ቤል (ጆን ቤል) የተባለውን እንግሊዛዊ የደጃዝማች ውቤን ጦር አሰፋፈር በመነፅር ዓይቶ እንዲነግራቸው ጠይቀውት ነበርና የደጃዝማች ውቤን ጦር አሰፋፈርና ድንኳን ዐይቶ በነገራቸው ጊዜ ‹‹አያሳድረኝ አላሳድረውም! … እንኳን ይህን ቁርጥማታም ሽማግሌ ይቅርና ወሎን መትቼ የሸዋውን ንጉሥ እይዘዋለሁ፤ ወታደር ሆይ ‹የውቤ ነፍጥ የውቤ ነፍጥ› ቢሉህ የተለጎመው ጨርቅና ባሩድ ነው፤ አይነካህም፤እኔ የክርስቶስ ባርያ ሁሉንም ዐሳይሃለሁ! … ‹ስሜን በስሜን እነግርሃለሁ› ያልኩህ ወታደር ሁሉ ስሜ ቴዎድሮስ ነው›› ብለው ፎክረው ተነሱና ጦርነቱ የካቲት 3 ቀን 1847 ዓ.ም ‹‹ቧሂት›› በተባለ ቦታ ላይ ተጀመረ፡፡ - - - ጦርነቱ ተፋፋመና ደጃዝማች እሸቴ የተባሉት የደጃዝማች ውቤ ልጅ ተመትተው ሲወድቁ የደጃዝማች ውቤ ጦር ሽሽት ጀመረ፡፡ ብላታ ኮከቤ የተባለው የደጃዝማች ውቤ የጦር አዝማችም አለቃውን ከድቶ ከነጭፍራው ወደ ደጃዝማች ካሣ ዞረ፡፡ ደጃዝማች ውቤም ቆስለው ተማረኩና ድሉ የደጃዝማች ካሣ ኃይሉ ሆነ፡፡ ደጃዝማች ካሣም ተሸናፊውን ደጃዝማች ውቤን ‹‹እኔ እሳቱ የመይሳው ልጅ! … አንተ ቆፍጣጣ (ጎባጣ) ቁርጥማታም ሽማግሌ አክብሬህ ‹ገብር› ብዬ ብልክብህ ምነው ሰደብከኝ? አሁንም ነፍጤንና ገንዘቤን አግባ!›› አሏቸው፡፡ ደጃዝማች ውቤም ‹‹እግዜር ያሳይዎ የነበረኝ ነፍጥና ገንዘብ ሁሉ አንድም ሳያመልጥ ከእጅዎ ገባ፤ ሌላ ምን አለኝ?›› ብለው መለሱላቸው፡፡ ደጃዝማች ውቤ ቤቴል (አምባ ጠዘን) በሚባለው ቦታ ያከማቹት እጅግ በጣም ብዙ ወርቅ፣ ብር (40ሺ ማርትሬዛ)፣ ጥይት፣ ጠመንጃ (ሰባት ሺ)፣ አህያ፣ ፈረስ፣ ግመል፣ ላም፣ በግ፣ ፍየል፣ በወርቅ የተለበጡ አልባሳት፣ የከበሩ ጌጣጌጦችና፣ ውድ ምንጣፎችና ሌሎች እቃዎች ተገኙ፡፡ በዚህ ጊዜም ደጃዝማች ካሣ የታሰሩትን ደጃዝማች ውቤን አስጠርተው ‹‹ይኸን ሁሉ ሀብት የሰበሰብከው ምን ሊሰራልህ ነው?›› ሲሉ ጠየቋቸው፡፡ ደጃዝማች ውቤም ‹‹ለክፉ ቀኔ እንዲሆነኝ ብዬ ነው›› አሏቸው፡፡ ደጃዝማች ካሣም ‹‹ሰው ያለውን ሀብት ከተጠቀመ ምን ክፉ ቀን አለ?›› በማለት መለሱና ወደ እስር ቤቱ እንዲመለሱ አዘዙ፡፡ ደጃዝማች ውቤም ከዓመታት በኋላ እስር ቤት ውስጥ ሞቱ፡፡ - - - በመጨረሻም … ‹‹የኮሶ ሻጭ ልጅ›› ተብለው የተናቁት… ‹‹… ደግሞ ለቆለኛ አንድ ወርች ስጋ ምን አነሰው?›› ተብለው በአማቶቻቸው የተቀለደባቸው … ካሣ ኃይሉ … ደጃዝማች ውቤ ኃይለማርያም ሊነግሱባት አስጊጠው ባሰሯት ደረስጌ ማርያም ቤተ-ክርስቲያን የካቲት 5 ቀን 1847 ዓ.ም በጳጳሱ በአቡነ ሰላማ እጅ ተቀብተው፣ ‹‹ዳግማዊ ቴዎድሮስ ንጉሰ ነገሥት ዘኢትዮጵያ›› ተብለው የኢትዮጵያ ንጉሥ ሆኑ! ዕለተ ሞት ፳፻፭ ዓ/ም - አንጋፋው ድምጻዊ ታምራት ሞላ በዚህ ዕለት አረፈ። ዋቢ ምንጮች መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፣ ዕለታዊ የታሪክ ድርጊት - “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያው ፓትረያርክ” (፲፱፻፶፩ ዓ/ም) የቴዎድሮስ ታሪክ፣ በብርሊን እንደሚገኝ አብነት፣ አሳታሚው ዶክቶር እኖ ሊትመን። በ፲፱፻ ወ ፪ ዓመት አጤ ቴዎድሮስና የኢትዮጵያ አንድነት (ተክለፃዲቅ መኩሪያ) አጤ ቴዎድሮስ (ጳውሎስ ኞኞ) የኢትዮጵያ የአምስት ሺ ዓመታት ታሪክ፡ ከኖህ-ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ፡ መጽሐፍ ፩ (ፍስሃ ያዜ ካሣ)
31174
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B3%E1%8A%95%E1%8C%89%E1%8A%95%20%E1%8B%8B%E1%8A%95%E1%8C%88%E1%88%9D
ዳንጉን ዋንገም
ዳንጉን ዋንገም በኮርያ ልማዳዊ አፈ ታሪክ በኮሪያ በጥንት የነገሠ ንጉሥ ነበር። እርሱ ከሺንሺ መንግሥት (ፔዳል) ቀጥሎ የአዲስ መንግሥት መሥራች ሆነ። የዚህ መንግሥት ስም «ጆሰን» ሲሆን፣ በኋላ ዘመን (ከ14ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም.) ሌላ «ጆሰን» የተባለ መንግሥት ስለ ኖረ፣ ዳንጉን የመሠረተው መንግሥት አሁን «ጥንታዊ ጆሰን» ወይም «ጎጆሰን» በመባል ይታወቃል። የፔዳል (ጸሐይ) ወገንና የናቱ ወገን «የድብ ጎሣ» በውሕደታቸው የጆሰን ብሔር ሆነው ዳንጉን እንደ ኮርያ መሥራችና አባት ይቆጠራል። ይህ በቻይና (ኋሥያ) ንጉሥ ያው 25ኛው ዓመት እንደ ሆነ ይታመናል። ዋና ከተማው አሳዳል ምናልባት የአሁኑ ፕዮንግያንግ፥ ወይም ሓርቢን በማንቹርያ ነበር። ከዚህ በላይ ዳንጉን የራሱን አምልኮት እንደ ዐዋጀ ይባላል፤ እስከ ዛሬም ድረስ ዳንጉንን እንደ አምላክ የሚቆጠሩ አንዳንድ ትንንሽ ሃይማኖቶች በኮርያ አገር አሉ። በጠቅላላ ለ93 ዓመታት (ወይም ለ1500 ዓመታት በአንድ ትውፊት) እንደ ነገሠ ይጻፋል። ከዚያ በኋላ ልጁ ቡሩ ተከተለው። በኋንዳን ጎጊ በ1903 ዓም. በኮሪይኛ የተዘጋጀው ዜና መዋዕል ኋንዳን ጎጊ ስለዚሁ አፈታሪካዊ ዘመን መረጃ ይሰጣል፤ ሆኖም በብዙ የኮርያ መምህሮች ዘንድ ይህ መጽሐፍ እንደ ትክክለኛ ታሪክ አይሆንም። ስለ ዳንጉን ዋንገውም ወይም ኢምግም ዘመን እንዲህ ይለናል። ዳንጉን ከአባቱ የሺንሺ ንጉሥና ከእናቱ የዉንግ ንግሥት ከልምጭ ዛፍ በታች ተወለደ (ምናልባት 2145 ዓክልበ. ግድም)። የአምላክ ምግባር ስለነበረው ሰዎች ሁሉ አከበሩት ታዘዙለትም፣ እድሜው 14 ዓመት ሲሆን፣ እናቱ የደዕብ ክፍላገር መስፍን አደረገችው። በ2108 ዓክልበ. ግድም የኮርያ ሰዎች (800 ሰዎች) በልምጭ ቦታ በሥነ ስርዓት ዙፋኑን ለዳንጉን ሰጡት። የሕዝቡ አለባበስ ያንጊዜ ከሣር ተሠራ፣ ጫማ ግን አልለበሱም ነበር ይላል። የዳንጉን ዐዋጅ እንዲህ ነበር፦ «ወደ ገነት (መንግስተ ሰማያት) የሚወስደው በር አንድ ብቻ ነው እንጅ ሁለት በሮች አይደሉም። መንፈስህ በሥራህ ላይ ብታኖረው፣ ያንጊዜ መንፈስህ ወደ ገነት ሊደርስ ይችላል። የገነት ሕግ አንድያ ሕግ ነው፣ እንደ ወትሮ ይቀጥላል፣ የሰውም አዕምሮ እንዲህ የሚቀጥል ነው። እንግዲህ ማንም ሰው የራሱን አዕምሮ ቢመረምር የሰውን አዕምሮ መመልከት ይችላል። ሰውዬው ሌሎቹን ከአምላክ ሕግ ጋር እንዲስማሙ ቢያስተምራቸው፣ ትምህርቱ በዓለሙ የትም ቦታ በትክክል ሊጠቀም ይችላል። ወላጆቻችሁና አያቶቻችሁ ከገነት (መንግስተ ሰማያት) ተወለዱ፣ እናንተም ያለነርሱ በሕይወት መኖር አትችሉም። ስለዚህ ወላጆቻህን ለማዳገፍና ለማገልገል ግዴታ አለብህ፣ ይህም ገነትን ማክበር ነውና ብሄሩን በሙሉ ይነካል። ወላጆችህንም የምታገልግላቸው ለብሔሩ በመታመንህ ነው። ይህንን ሕግ በመጠብቅ ብቻ ከድንገተኛ አደጋ ወይም ከመዓት ማምለጥ የሚቻል ነው። እንስሳ ስንኳ የኑሮ ጓደና አለው፣ የተቀደደውም ጫማ ጥንዱን አለው። እንዲህ ወንድና ሴት በሰላም ያለ ጠብ፣ ቅሬታ ወይም መቀኝነት ይኖራሉ። ደግሞ መረንነትና ዝሙት ክልክል መሆን አለባቸው። ጣቶችህን ብትነክስ፣ የትኛው ጣት መጠኑ ምንም ቢሆን ሕመም አያሰኝህም? እያንዳንዳችሁ ከሐሜት ስትቀሩ፣ እርስ በርስ ስትዋደዱ፣ ከጠብ ስትቀሩ፣ ሌሎቹንም ስትረዱአቸው፣ ያንጊዜ መላው ብሐሩና መላው ቤተሠቡ ደህና ይሆናሉ ይበልጸጋሉ። ላሞችና ፈረሶቻቸሁ መኖአቸውን በጋራ ያከፋፍላሉ። ሰውን ከምንም ነገር ካላሳጣችሁ፣ ያለ ሌብነት ከተባበራችሁ፣ አገሩ ሁሉ ይበልጸጋል።... ሁልጊዜ በገነት (መንግሥተ ሰማያት) አክባሪ አዕምሮ ውደዱ። ሰው በአደገኛ ሁኔታ ስታገኘው፣ እሱን መርዳት እንጂ ሌሎችን መሳድብ የለብህም። እኒህን ድንጋጌዎች ካልታዘዝክ፣ ገነት (መንግሥተ ሰማያት) አይረዳህም፣ አንተና ቤተሠብህ እስከሚጠፋ ድረስ። እሳት በሩዝ እርሻ ላይ ብታደርግ፣ የሩዙም ተክል ቢቃጠል፣ ገነት (መንግሥተ ሰማያት) ይቀጣሃል። ጥፋተኛ ብትሰውረውም፣ የወንጀሉ ክርፋት ግን ይወጣል። ሁልጊዜ በጎ ጸባይ በአክባሪ አዕምሮ ትይዛለህ። ክፉ አዕምሮ አይኖርህ፣ ጥፋትን አትደብቅ፣ አደጋንም አትሰውር። አዕምሮህን በማሠልጠን ገነትን (መንግሥተ ሰማያትን) አክበር፤ ለመላውም ሕዝቡ ጓደኛ ሁን። አምስቱ ዋና ሚኒስትሮች እኒህን ድንጋጌዎች መጠብቅ አለባቸው።» ከዚህ በኋላ ከሚኒስትሮቹ ፐንግ-ዉ ምድረ በዳ እንዲያቀና፣ ሰውንግጁ ቤተ መንግሥት እንዲያሠራ፣ ጎሺ በእርሻ ተግባር ላይ፣ ሺንጂ ምስሎችን እንዲፈጥር፣ ኪሰውንግ በሕክምና ጥናት ላይ፣ ነዑል ቤተሠቦቹን በዝርዝር እንዲዘግብ፣ ኸዊ እድሎችን (በንግር) በመናገር ላይ፣ ዉ በጦር ሠራዊት ላይ ሾማቸው። በ2059 ዓክልበ. ግድም በታላቅ ጐርፍ ምክንያት የሕዝቡ ምቾት ተበላሸ። ስለዚህ ዳንጉን ሚኒስትሩን ፐንግ-ዉ ወንዞቹን እንዲገድብ አዘዘው። ሐውልት በ«ዉ» መንደር ተሠራ። በ2058 ዓክልበ. ሚኒስትሩን ፐዳል አምባ በሳምላንግ እንሲያሠራ አዘዘው። በ2042 ዓክልበ. ግድም አልጋ ወራሹን ልዑል ቡሩ በተልእኮ ወደ ዩ ላከው፣ ይህ ምናልባት በኋላ ዳ ዩ የተባለው የኋሥያ (ቻይና) አለቃ ይሆናል። በተጨማሪ ዳንጉን የ፭ ንጥረ ነገሮች ትምህርት አስተማረ፣ «ዩጁ» እና «ያንግጁ» ግዛቶችም ወደ ጆሰን ጨመረ። ዳንጉን ደግሞ «ኈዳይ»ን አሸንፎ ተገዥ አደረገው፣ ዩ-ሹን በተገዥነት አስተዳዳሪነቱን ሰጠው ይለናል። «ዩ-ሹን» ማለት የኋሥያ ንጉሥ ሹን ስም ነው፤ «ኈዳይ»ም በሻንዶንግ ልሳነ ምድር እንደ ነበር ይታስባል። በ2016 ዓክልበ. ግድም ለሀብቱ እድገት መስኖ፣ የሐር ትል፣ እና የአሣ ማጥመድ ሥራ ክፍሎች ወደ ጆሰን አስገባ። ዳንጉን ኢንገም በአገሩ ለ93 ዓመታት ነግሦ አረፈ፣ ልጁም ዳንጉን ቡሩ ያንጊዜ የጆሰን ዳንጉን (ንጉሥ) ሆኖ ተከተለው።
16096
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%9E%E1%88%AB%E1%88%B5%E1%89%B0%E1%88%AD%20%E1%8D%8D%E1%8A%AB%E1%88%AC
የዞራስተር ፍካሬ
የዞራስተር ፍካሬ: ወደ ሁሉምና ወደ ማንም በፍሬድሪች ዊልሄልም ኒሺ የተደረሰ የፍልስፍና ልቦለድ* ነው። መጽሐፉ በ1883 እና 1885 (እ.ኤ.አ) መካከል በ4 ክፍል የተደረሰ ሲሆን በጊዜው ይሰራበት ከነበረው የአስተሳሰብ ዘዴ ለየት ባለ መልኩ የፍልስፍናን እና የግብረገብን ጥናቶች መርምሯል። የመጽሃፉ አትኩሮቶች፡- የዘላለማዊ ምልልስ፣ ኃይልን መፍቀድ (*ፈቃድ እዚህ ላይ ጠንካራ ፍላጎት ማለት ነው)፣ የአምላክ በጊዜው በነበሩ አውሮጳውያን ልብ ውስጥ መሞት፣ ስለዚህም የአዳዲስ ዋጋ ወይም ህግጋት አስፈላጊነት፣የበላይ ሰው (*በኒሺ አስተሳሰብ የሰው ልጅ በጦጣዎችና በበላይ ሰው መካከል ያለ ፍጡር ነው) መምጣት ትምህርቶች ነበሩ። ጽሁፉ የመጽሐፍ ቅዱስ አጻጻፍ ስልት ይከተል እንጂ የውስጡ ፍሬ ነገር ግን የክርስትናና አይሁድ ሃይማኖቶችን መሰረታዊ እምነቶች የሚጻረር ነበር። ኒሺ ይህን መጽሐፍ " ከሰዎችና ከጊዜ 6000 ጫማ" እርቆ እንደጻፈ ይናገራል፣ ማለቱም የመጽሃፉን ሃሳቦች በተራራ ላይ እያለ እንዳገኛቸው ለማስገንዘብ ነበር። ኒሺ "የዞራስተር ፍካሬ" ብሎ የሰየመውን መጽሃፍ "ስርዓት አልባ"(ጥራዝ ነጠቅ) በሆነ ዘዴ ስለጻፈው ለተመራማሪወች እጅግ አስቸጋሪ ሆነ። ይሁንና ተመራማሪወች አንድ አንድ ቋሚ የሆኑ የመጽሃፉን ይዘቶች ማስተዋላቸው አልቀረም፦ የበላይ ሰው፡ ለኒሺ የበላይ ሰው ማለት በራሱ ላይ ሙሉ ቁጥጥር ያለው ግለሰብ፣ እምቅ ኃይሉን ወደ ስራ የተርጎመ ሰው ማለት ነው። አሁን ያለው የሰው ልጅ (በኒሺ አሰተያየት) በእንስሳ እና በዚህ በበላይ ሰው መካከል ያለ ፍጡር ነው። የዘላለም ምልልስ፡ ማናቸውም የተከሰቱ ነገሮች እንደገና ይከሰታሉ፣ አሁን የሚከሰቱ ነገሮች ድሮም ተከስተው ነበር ለወደፊቱም እልፍ አዕላፍ ጊዜ ይከሰታሉ! ይህ አለም ልክ እንደምናየው ሆኖ እንደገና ይከሰታል፣ ሰውም ይሞታል ግን ልክ በነበረበት መልኩ በነበረበት አለም ተመልሶ ይመጣል። ኅይል መፍቀድ፡ የሰው ተፈጥሮ መሰረታዊ ባህርይ ነው። ማናቸውም የምንሰራቸው ነገሮች፣ እንደ ኒሺ አስተያየት፣ የዚህ መሪ ሃሳብ መገለጫ ናቸው። ከመራባት፣ ደስታ፣ ሐሴት ጋር ሲነጻጸር የበለጠ መሰረታዊ ሲሆን የኅይል መፍቀድ ሁሉም ህይወት ያለው ነገር ሁሉ ከከባቢው አለም ጋር የሚያደርገውን ትግል ጠቅልሎ የሚይዝ ጽንሰ ሃሳብ ነው። በኃጥያትና ጽድቅ ስራወች በተሰኙ ተቃራኒ የክርስትና ሃሳቦች ላይ ብዙ ትችት መመስረት። በኒሺ አስተያየት እኒህ ነገሮች የሰው ልጅ ፈጠራወች እንጂ በተፈጥሮ የሚገኙ አይደሉም። በሱ አስተያየት የሰው ልጅ ተግባር መለካት ያለበት አስቀድሞ በተቀመጡ የግብረ ገብ ዋጋወች/ህጎች (ጥሩና መጥፎ) ሳይሆን የተግባሩን መዘዝ በመለካት ነው። መጽሐፉ ባጭሩ በመጽሃፉ መግቢያ ላይ ዞራስተር 30 አመት ሲሞላው ወደ ተራራ እንደወጣና በዚያ ከሰወች ተለይቶ ብዙ ጥበቦችን እንደሰበሰብ እናነባለን። 40 አመት ሲሞላው ያከማቸውን ጥበብ ለማካፈል ከተራራው ወረደ። የመውረዱ ዋና አላማ "የበላይ ሰው"ን መምጣት ለመስበክ ነበር። የበላይ ሰው፣ በዞራስተር አስተሳሰብ፣ ከሰው በላይ የሆነ ፍጡር ማለት ነው፡ ልክ የሰው ልጅ ከጦጣወች በላይ የሆነ ፍጡር እንደሆነ። በዞራስተር ግምት ዘመናዊው ሰው የወኔ ግሽበት፣ ባዶነትና አጠቃላይ የህይወት ውዥንብር ስለገጠመው አዲስ ትምህርት ያስፈልገዋል። በዞራስተር አስተሳሰብ የዘመናዊው ሰው መንፈሳዊ ግሽበት ምክንያት የአምላክ መሞት ነው። በርግጥ አምላክ ለመሞት አይቻለውም ሆኖም ግን በዞራስቶር አስተሳሰብ አምላክ ሞተ ማለቱ ዘመናዊው ሰው በአምላክ ላይ ያለው እምነቱ ሞተ ማለት ነው። ስለሆነም የድሮወቹ ሰወች ብዙ አስደናቂ ስራወችን ለአምላክ ሲሉ ቢሰሩም የዘመናዊው ሰው ግን ይህን እመንቱን በማጣቱ አጠቃላይ ዘመናዊ ህብረተሰብ መሪ ሃሳብ የማጣት፣ የመበስበስና ተስፋ የማጣት ምልክቶች አሳየ። ህግን የሚሰጥ በሰው አምሳያ ያለ አምላክ ለአዲሱ ሳይንሳዊና ዘምናዊ ህብረተሰብ እጅግ ኋላ ቀር መስሎ ታየ። ስለሆነም በተለይ በተማሩ ሰወች ዘንድ የአለም የህይወት ትርጉምና የግብረገብ ስርዓት እጅግ ዝብርቅርቅ ያለ ሆነ። ዘመናዊ ሰው ባዶነት "ኒሂልዝም"( የህይወት ትርጉም ማጣት) የሚባል ችግር ተጋረጠው፣ "የዞራስተር ፍካሬ" ዋና አላማ ይህን ባዶነት መታገል ነበር። በኒሺ አስተሳሰብ አዲሱ የ"በላይ ሰው" ትምህርት ለዚህ ዘመናዊ ኒሂሊዝም (ባዶነት) ፍቱን መድሃኒት መሆን ነበር። ዞራስተር ከተራራው ወርዶ በሰወች መካከል እንዲህ ሲል ሰበከ፡ የሰው ልጅ በአሁኑ ሰዓት ያለበትን መናኛነት (ተራነት)ና የከሰረ ስልጣኔ በማሸነፍ የ"በላይ ሰው"ን መፍጠር አለበት፡ «የሰው ልጅ ሊሸነፍ የሚገባ ነው። ለማሸነፍ እያንዳንዳችሁ ምን አድርጋችኋል?» ሆኖም ግን ይህ ሰበካው ተቀባይነት አጣ። ህዝቡም መልሶ «የበላይ ሰውህን እዚያው ለራስህ» ብለውም ተሳለቁበት። የተመቻቸና ጥሩ ኑሮ ከመፈለግ ውጭ የበላይ ሰውን እንደማይፈልጉ ነገሩት። ህይወት የበለጠ ትርጉም ካልተሰጠው በርግጥም ከደስታ ውጭ ምንስ ያስፈልጋል? በዚህ ምክንያት የስልጣኔ ዋና ዓላማ ተራ መናኛ ሆነ፣ እርሱም፡- "ከፍተኛ ደስታ ለከፍተኛ ቁጥር ላለው ሰው" ሆነ። ይህ ተራነት ዞራስተር ለህዝቡ ያለው ጥላቻና ንቀት እንዲያድግ አደርገ ( ምንም እንኳ ከጊዜ ወደጊዜ ሊያዝንላቸውና ሊረዳቸው ህሊናው ቢግደረደርም)። ተማሪውም ሆነ ያልተማረው፣ ፖለቲከኛውም ሆነ ፈላስፋው፣ ሰዓሊውም ሆነ ፕሮፌሰሩ፣ ሁሉም የተደላደለ ህይወት ከመሻት ውጭ ውስጣቸው ያለውን እምቅ ስብዕና ለማሳደግ የማይጥሩ ሆኖ አገኛቸው። ካደረበት ንቀት የተነሳ ዞራስተር ብዙ ተከታይ ከማፍራት ይልቅ ሊግባባቸው የሚችሉ ጥቂት ፈርጥ የሆኑ ሰወችን ፍለጋ ጀመረ፡ ተራ(መናኛ) ነገሮችን ከህይወት ለማግኘት የሚሞክሩን ሳይሆን፣ ከፍተኛ ነገርን ለማግኘት የሚሞክሩትን። ፍለጋው ጥቂት ሰወችን ስላስገኘለት ለኒህ ለተመረጡት "ማስተማር" በጥብቅ ጀመረ። የመጨረሻው የመጽሃፉ እትም 4 ክፍሎች አሉት። እያንዳንዱ ክፍል ለማብራራት ብዙ ቦታ ስለሚይዝ ከዚህ በታች በየራሳቸው ገጽ ማብራሪያቸው ሰፍሯል። ይመልከቱ። ክፍል ፩ ክፍል ፪ ክፍል ፫ ክፍል ፬ ከፍካሬ ዞራስተር የተወሰዱ ጥቅሶች ህይወትን የምናፈቅር መኖር ስለምናወቅ ሳይሆን ማፍቀር ስለምናውቅ ነው። በፍቅር ውስጥ ሁል ጊዜ ዕብደት አለ። በዕብደት ውስጥ ደግሞ ሁልጊዜ ምክንያት አለ። አንቺ ታላቅ ኮከብ! ፍንትው ብለሽ የምታበሪላቸው ባይኖሩ ደስታሽ ምኑ ላይ ነበር? መብረርን የሚማር መጀመሪያ መቆምን፣ ከዚያም መራመድን፣ ብሎም መሮጥንና ዛፍ መውጣትን እንዲሁም መደነስን መማር አለበት፣ ወደ መብረር መብረር አይቻልም! እውነትን መናገር - በጣም ጥቂት ሰወች ይችላሉ! ከነዚህ ከሚችሉት ግን የሚፈፅሙት የሉም`! ደፋርነት፣ ደንታ ቢስነት፣ አላጋጭነት፣ ጸበኛነት-- ጥበብ ከኛ እኒህን ትፈልጋለች፡ ሴት ናትና የምትወደውም ጦረኛን ብቻ ነው። እራሱን የማያዝ መታዘዝ አለበት። ብዙወች እራሳቸውን ማዘዝ ይችላሉ፣ ነገር ግን ለራሳቸው ከመታዘዛቸው በፊት ብዙ ይጎላቸዋል! ህብረተሰብ ተኩላውን አላምዶ ውሻ አደረገ። የሰው ልጅ ከሁሉም የሚበልጥ ለማዳ እንስሳ ነው! አንድ ልምድ አጀማመሩ በሩቅ የዘመን ጭጋግ እየተሸፈነ ከሄደ፣ አመሰራረቱም እየተምታታ ከመጣ -- በክብር እያደገ ይሄዳል። ከትውልድ ወደ ትውልድም ክብሩ እየጨመረ ይሄዳል። በመጨረሻ ልምዱ ቅዱስ ይሆንና በሰወች ዘንድ ድንቅ ይሆናል። ሰው በንዴት አይገድልም፣ በሳቅ እንጂ። በቁመና ለማደግ፣ ወደብርሃንም ለመጠጋት በተፈለገ ጊዜ፣ ስርን ወደ መሬት መላክ ያስፈልጋል፣ ወደ ድቅድቅ ጨለማው፣ ወደ ጥልቁ - ወደ መጥፎው። እውነተኛ ወንድ ሁለት ነገር ይፈልጋል፡- አደጋና ጨዋታ። ለዚያ ሲልም ሴትን ይፈልጋል፣ ከሁሉ በላይ አደገኛ የሆነች መጫወቻ። "የታላላቆቹ ተራሮች አመጣት ከየት ይሆን?" ብየ ጠይኩ። ከባህር እንደመጡ ደረስኩበት፣ ማስረጃውም በአለቶቻቸውና በከፍተኛ ገጽታቸው ተጽፎ ይገኛል። ታላላቅ ከፍታወች የሚመጡት ከታላላቅ ጥልቀቶች ነው። ነጻ ከምን? ለዞራስተር ደንታ ይሰጠው ይመስል! ይልቁኑ ብሩህ አይኖችህ እንዲህ ይበሉ፡ ነጻ ምን ለማድረግ? ሳንደንስበት ያለፈን ቀን እንደጠፋ ቀን መቁጥር ይገባል። እንዲሁ በሳቅ ያልታጀበን እውነት ውሸት ማለት ይገባል። መተኛት ቀላል ጥበብ አይደለም፡ ለዚህ ተግባር ሲባል ቀኑን ሙሉ መንቃት ግድ ይላል። መደብ : የዞራስተር ፍካሬ መደብ :ፍልስፍና መደብ :ኒሺ ሥነ ጽሁፍ
45625
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%B3%E1%8B%AD%E1%8A%95%E1%88%B5%E1%8A%93%20%E1%89%B4%E1%8A%AD%E1%8A%96%E1%88%8E%E1%8C%82%20%E1%88%98%E1%88%A8%E1%8C%83%20%E1%88%9B%E1%8B%95%E1%8A%A8%E1%88%8D%20%28%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%29
የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል (ኢትዮጵያ)
የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል (ሳ.ቴ.መ.ማ.)፣ ኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎችን የመሰብሰብ፣ የመምረጥ፣ የመተንተንና እሴት አክሎ የማሰራጨት ኃላፊነት የተጣለበት የመንግስት ድርጅት ነው። የአመሰራረት ታሪክ በኢትዮጵያ ውስጥ ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎች ስብስብ ማዕከልን ለማቋቋም የመጀመሪያውን ሀሳብ የወጠነው በ1977 እ.ኤ.አ. የኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን (ኢ.ሳ.ቴ.ኮ) ነበር። ኢኒስቲቲዩቱ የተመሰረተበት ዋነኛ ዓላማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎችን ለመሰብሰብ፣ ለማደራጀት እና ለማሰራጨት የሚያስፈልጉ የተለያዩ አገልግሎቶችንና መገልገያ ቁሳቁሶችን ለማቅረብ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ነው። ዋና መቀመጫውን አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ልዩ ስሙ ቡልጋሪያ ማዞሪያ ያደረገው የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል (ሳ.ቴ.መ.ማ) በማቋቋሚያ ደንብ ቁጥር 257/2004 የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎችን በማፈላለግ፣ በመሰብሰብ፣ በመመምረጥ፣ በማደራጀት፣ በመተንተን እና በጥናትና ምርምር እሴት ጨምሮ በማሰራጨት የሀገሪቱን የቴክኖሎጂ ሽግግር ሂደት የማፋጠን ተልዕኮን በመያዝ የተመሰረተ ነው። የማዕከሉ ስትራቴጂክ መሰረቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ በመንግስትና በሕዝብ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በላቀ ብቃት ለማሳካት የተልዕኮ አፈፃፀም አቅጣጫ ጠቃሚ ኮምፓሶች የሆኑት ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ እሴቶችና ተቋማዊ ፍልስፍናዎች (ስትራቴጂክ መሰረቶች) ያስፈልጉታል። በመሆኑም የማዕከሉ ስትራቴጂክ መሰረቶች እንደሚከተለው ቀርቧል። • በ2015 ዓ.ም የኢንፎርሜሽን ማኅበረሰብ ለመፍጠር የሚያስችል የሳይንስና ቴክኖሎጂ ልዕቀት ማዕከል ተገንብቶ ማየት፤ • ቴክኖሎጂን ለልማት ለመጠቀም በሚደረግ ጥረት ዘላቂ የኢንፎርሜሽን ምንጭ መሆን፤ • የባለቤትነት ስሜት • መደመር • ተማሪነት ተቋማዊ ፍልስፍና • መረጃችን ለሀገራዊ ቴክኖሎጂ ምጥቀት፤ • ተቋማዊ ልዕቀታችን በሰው ኃይላችን፤ • እሴት በማከል እንተማለን፤ ተቋማዊ አወቃቀር ዳይሬክቶሬት • የምርምርና ትንተና ዳይሬክቶሬት • የእውቀት አስተዳደርና ስርጭት ዳይሬክቶሬት • የኢንፎርሜሽን መሰረተ ልማት ዳይሬክቶሬት የኢትዮጵያ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲ የኢትዮጵያ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲ በ2004 ዓ.ም የፀደቀ ሲሆን ሀገሪቷ ውጤታማ የሆኑ የውጭ ቴክኖሎጂዎችን ለማፈላለግ፣ ለመምረጥ፣ ለማስገባት እንዲሁም ለመጠቀም የሚያስችላትን ሀገራዊ የኢኖቬሽን ስርዓት ለመፍጠርም ያለመ ነው። የፖሊሲው ዓላማ ውጤታማ የሆኑ የውጭ ቴክኖሎጂዎችን በማፈላለግ፣ በመምረጥ እና በማስገባት በማምረቻና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥ የመማር፣ የማላመድ እና የመጠቀም ሀገራዊ አቅም ለመገንባት የሚያስችል የቴክኖሎጂ ሽግግር ማዕቀፍ መፍጠር ነው። የሀገሪቷን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ችግሮች ጥናትና ምርጥ ተሞክሮ ያላቸው የሌሎች ሀገራት ሁኔታ ላይ የዳሰሳ ጥናት የተካሄደ ሲሆን በዚህም መሰረት አስራ አንድ ወሳኝ የፖሊሲ ጉዳዮች ተለይተዋል። እነዚህም፡- የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የማምረቻና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ ምርምር፣ የፋይናንስ ሥርዓትና ማበረታቻ ሥርዓት፣ ብሔራዊ የጥራት መሰረተ ልማት፣ የዩኒቪርሲቲዎች፣ የምርምር ተቋማት፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማትና የኢንዱስትሪ ትስስር፣ የአዕምሯዊ ንብረት ሥርዓት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ፣ የአካባቢ ልማትና ጥበቃ እንዲሁም ዓቀም አቀፍ ትብብር ናቸው። ሀገራዊው የኢኖቬሽን ሥርዓት አስተዳደር መዋቅር የፖሊሲውን አፈፃፀም ለመምራት፣ ለመደገፍ እና ለመከታተል እንዲያስችል ተዘርግቷል። የኢኖቬሽን ሥርዓቱ ዋና ዋና ተዋናዮችም፡- ሀገራዊው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምክር ቤት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ሌሎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እንዲሁም የኢኖቬሽን ድጋፍና የምርምር ሥርዓት ናቸው። የኢንፎርሜሽን ስርጭት የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል አንዱ ቁልፍ ተግባር እሴት የታከለባቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃዎችን ማሰራጨት ሲሆን እነዚህን መረጃዎች ለማሰራጨት ማዕከሉ የተለያዩ የማሰራጫ ስልቶችን ይጠቀማል። ከስልቶቹ መካከል የቴሌቪዥን ስርጭት፣ ድረ-ገፅ ወይም የሳይበር እና የህትመት ሚዲያን ይጠቀማል። ማዕከሉ በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ቴክ-ሳይንስ የተሰኘ መጽሐፍን በሶስት ወር አንድ ጊዜ የሚያሳትም ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ በሳምንት አንድ ቀን ለ30 ደቂቃ ቆይታ የሚያደርግ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አለው። ይህ የቴሌቪዥን ፕሮግራም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢ.ቢ.ሲ) የቴሌቪዥን ጣቢያ የሚሰራጭ ነው። ሌላው መረጃ የማሰራጫ ስልት የሳይበር ሚዲያ ሲሆን ማዕከሉ የራሱ የሆነ ድረ-ገፅን (/ ወይም ) ይጠቀማል። ይህ ድረ-ገፅ በየቀኑ ከዓለማችን የተሰበሰቡና እሴት የታከለባቸው የተለያዩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዜናዎችን የያዘ ሲሆን በተጨማሪም የተለያዩ የምርምር ጥናቶችንና ህትመቶችን የያዘ ነው። የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካቾች የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካቾች ስለ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስርዓት፣ ዉስጣዊ መዋቅር፣ ከኢኮኖሚና ከማኅበረሰብ ጋር ስላለው ትስስር እንዲሁም ስርዓቱን የሚያስተዳድሩ አካላት፣ በውስጡ እንቅስቃሴ ለሚያደርጉ እና ስርዓቱ ተፅዕኖ ለሚያደርስባቸው አካላት ጥያቄዎችን የሚመልሱ ተያያዥነት ያላቸው መረጃዎች ናቸው። ይህ የሚያመላክተው በብሔራዊ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስርዓት ላይ የሚመጣ ለውጥ በአምራችና አገልግሎት ሰጪ (የንግድ ተቋማት)፣ ተመራማሪዎች፣ የመንግስት ኤጀንሲዎች፣ በዘርፉ የሚሳተፉ ባለድርሻ አካላት መካከል ያለ ትስስርና ግንዛቤ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንደሚያመጣ ነው። የምርምርና ስርፀት ሰርቬይ ምርምርና ስርፀት አንዱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ነው። ይህ አመላካች አዲስ ግኝቶችን ለመፍጠር የሚያስችሉ የዕውቀት ክምችትን እድገት፣ ከግለሰቦች የሚገኝን፣ ከባህልና ከማኅበረሰብ የሚገኝን እውቀት የሚያካትት እንዲሁም የዕውቀት ክምችትን መጠቀምን የሚያጠቃልል ነው። የመጀመሪያው ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ዳሰሳ ጥናት በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በ2010 እ.ኤ.አ. የተካሄደ ሲሆን በ2013 እ.ኤ.አ. ሳ.ቴ.መ.ማ ኃላፊነቱን ወስዶ ሁለተኛውን ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ዳሰሳ ጥናት በማከናወን የጥናቱን ውጤት በ2014 እ.ኤ.አ. አውጥቷል። ዳሳሳ ጥናቱ ሀገሪቱ በምርምርና ስርፀት ላይ ያላትን ኢንቨስትመንትና የሰው ኃይል አግባብ በአራት ዘርፎች ከፋፍሎ የሚያሳይ ጥናት ነው። የመንግስት ተቋማት፣ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ የቢዝነስ ተቋማት እና የግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጥናቱ የዳሰሳቸው ዘርፎች ናቸው። በ2014 እ.ኤ.አ. የታተመው ጥናት በዋነኛነት ሀገሪቱ ለምርምርና ስርፀት የምታወጣው ወጪ ከሀገሪቱ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ምን ያህል እንደሆነ ለመጠቆም ነው። ከጥናቱም የተገኘው ውጤት እንደሚያመለክትው የምርመርና ስርፀት ወጪ የሀገሪቱን አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት 0.6 በመቶ ነው። ይህም በአፍሪካ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት 1 በመቶ የሚሆነውን ወጪ ለምርምርና ስርፀት ማዋል ተብሎ የተቀመጠውን አቅጣጫ የሳተ ውጤት እንዳልሆነ ለመገንዘብ ተችሏል። በተጨማሪም በ2010 እ.ኤ.አ. ከተከናወነው ጥናት ውጤት ጋር ሲነፃፀር አመላካቹ (0.24 በመቶ) በ3 እጥፍ እድገት አሳይቷል። የኢኖቬሽን ሰርቬይ ኢትዮጵያ ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋገርና የተጀመረውን የልማት ጎዳና ቀጣይነት ባለዉ መልኩ ለማስኬድ እውቀት መር ኢኮኖሚ ልትከተል ይገባል። በእውቀት መር ኢኮኖሚ ኢኖቬሽን ቁልፍ ሚና ይጫወታል። ይህንንም በመገንዘብ በሀገሪቱ ውስጥ ያለዉን የኢኖቬሽን ደረጃ ለመገንዘብና ተቋማት ለኢኖቬሽን እንቅስቃሴዎች የሚያወጡትን ወጪና ከተለያዩ ተቋማት ጋር እውቀትንና ክፍሎትን ለማዳበር የሚያደርጉትን ግንኙነቶች ለመረዳት እንዲሁም ዘርፉን ለማስተዳደር የሚችል ፖሊሲ ለመቅረፅ በ2007 የመጀመሪያውን የኢኖቬሽን ሰርቬይ ለማካሄድ ታቅዷል። ይህንንም እንዲያከናውን የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል ሙሉ ሀላፊነት ተጥሎበታል። ማዕከሉ የንግድ ተቋማትን እንደዋነኛ የጥናት ክፍል በመውሰድ በአራት ዘርፎች ላይ፣ ከዘጠኙ ክልሎችና በሁለቱ የፌደራል ከተማ መስተዳድሮች ውስጥ በናሙና የተመረጡ ተቋማት በሚያመርቷቸው ምርቶች ላይ፣ ከአመራረት ሂደት አንፃር፣ ከተቋም አስተዳደር እና ከግብይት ስርዓት አንፃር የሚያከናውኗቸው ኢኖቬሽኖች ላይ ጥናት ሊያከናውን አቅዷል። ተቋሙ ጥናቱን በሀምሌ 2006 ጀምሮ በሰኔ 2007 ዓም የሚያጠናቅቅ ሲሆን አሁን ማለትም በሚያዚያ ወር ላይ የጥናቱ 90 በመቶ ተገባዷል። የሳይንስና ቴክኖሎጂ አመላካች ተብለው ከሚጠቀሱት ውስጥ ሌላው ቢብሎሜትሪክስ ነው። ቢብሎሜትሪክስ የጥናታዊ ፅሁፍ ህትመቶችንና ማጣቀሻዎቻቸውን አህዛዊ ትንተናና ስታስቲክስን በመጠቀም የሚለካ ነው። ቢብሎሜትሪክስ ስታትስቲካዊ ትንተና በመጠቀም የማጣቀሻና የቃላት ድግግሞሽ ትንተና በማከናወን መረጃዎች አቅጣጫ ማግኘት ነው። የህትመቶችንና የማጣቀሻዎቻቸውን አህዛዊ ልኬትን በመጠቀም መለካት በመላው ዓለም ጥቅም ላይ እየዋለ ያለ አካሄድ ነው። ቢብሎሜትሪክስ የጥናቶችን አቅም ለመለካት ጥቅም ላይ ይውላል። ቢብሎሜትሪክስን የጥናቶችን አቅም ለመለካት ከሚጠቀሙ መካከል ዩኒቨርሲቲዎችና የመንግስት ላቦራቶሪዎች፣ ፖሊሲ የሚቀርፁ አካላት፣ የምርምር ዳይሬክተሮችና አስተዳደሮች፣ የመረጃ ልዩ ሙያተኞች እና ላይብረሪያኖች እንዲሁም የምርምር ባለሙያዎች ዋነኞቹ ናቸው። እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ የቢብሎሜትሪክስ ትንተና በሀገሪቱ የጥናት ባለሙያዎች አልተከናወነም። የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል በ2014 እ.ኤ.አ. የቢብሎሜትሪክስ ትነተና ለማከናወን ዕቅድ ይዟል። የአይ.ሲ.ቲ ሲስተሞች • ዌብ መሰረት ያደረገ የሰው ኃይል አውቶሜሽን ሲስተም በማዕከሉ ውስጥ የሚኖረው የሰው ኃይል አስተዳደር ስራ የተማከለና በአንድ መስኮት የሚከናወን ለማድረግ ምቹ የሆነ፣ የሰራተኞችን ማህደር በመያዝ ሰራተኞች የግል መረጃዎቻቸውን ማየትና ማስተካከል እንዲችሉ የሚረዳ ሲስተም ነው። • ዌብ መሰረት ያደረገ የእውቀት አስተዳደርና ኢለርኒንግ ሲስተም በማዕከሉ በሚገኙት ሰራተኞች ዉስጥ የሚኖርን እውቀት ተደብቆ እንዳይቀር እርስ በእርስ የመማሪያና የእውቀት መገበያያ መድረክ በመሆን የሚያገለግል ሲስተም ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ በተለያዩ መንገዶች የተሰበሰቡ እውቀቶችን ከማዕከሉ ዉጪ ለሚገኙ ተጠቃሚዎች ለማጋራት አመቺ ስፍራ የሚፈጥር ሲስተም ነው። • የመረጃ ማነፍነፊያ ሲስተም ይህ ጎልጉል የተሰኘው የመረጃ ማነፍነፊያ () ሲሆን መንግስት ትኩረት በሰጠባቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች መረጃዎችን ኢንዴክስ በማድረግ የተጠቃሚዎችን የመረጃ ጥማት ለማርካት የተበለፀገ ሲስተም ነው። • የብሔራዊ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዲጂታል ላይብረሪ ሲስተም መንግስት ትኩረት በሰጠባቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ መስኮች ዙሪያ የሚገኙ መጽሐፍትን ተጠቃሚዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በኢንተርኔት እንዲያገኙ የሚያስችል ሀገራዊ ይዘት የተላበሰ ሲስተም ነው። • ዌብ መሰረት ያደረገ የአዕምሯዊ ንብረት ሲስተም በቴክኖሎጂ ሽግግሩ መንግስት ትኩረት በሰጠባቸው የትኩረት መስኮች የተሰበሰቡ የፓተንት መረጃዎች ለስራ ፈጣሪዎችና ተመራማሪዎች በሚያመችና ቀላል በሆነ ሀገራዊ ይዘትን በተላበስ መንገድ ማግኘት እንዲቻል የተበለፀገ ሲስተም ነው። • የ (ኦፕቲካል ካራክተር ሪኮግኒሽን) ሲስተም በህትመት መልክ የሚገኙ አማርኛን ጨምሮ በሌሎች ቋንቋዎች ያሉ ማንኛውም አይነት መረጃዎች ስካን ከተደረጉ በኋላ በቀላሉ በኮምፒውተር አማካኝነት መረዳትና መነበብ እንዲሁም ኤዲት መደረግ እንዲችሉ የሚያግዝ ሲስተም ነው። • የማዕከሉ ድረ-ገፅ በማዕከሉ የሚገኙትን ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ እውቀቶችና ትኩስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዜናዎችን ተደራሽ ለማድረግ ማራኪ ገፅታን ተላብሶና የተጠቃሚዎችን ፍላጎት መሰረት አድርጎ በአማርኛና እንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ድረ ገፅ ነው። • የማዕከሉ የውስጥ መገናኛ ኢንተርናል ፖርታል ይህ የዉስጥ ለዉስጥ መገናኛ በማዕከሉ ዉስጥ የሚገኙ ሰራተኞች የማዕከሉን መተዳደሪያ ሕግና ደንብ፣ ፖሊሲና መመሪያዎች እንዲሁም ማስታወቂያዎች በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችል፣ የማዕከሉን ወቅታዊ የስራ ሂደትና የሰራተኞች የአፈፃፀም ደረጃ የሚያሳይ ሲሆን በተጨማሪም ሰራተኞች እርስ በእርስ የሚኖራቸውን የስራ ግንኙነት በይበልጥ ለማጠናከር የሚያግዝ ሲስተም ነው። • ዌብ መሰረት ያደረገ ሲስተም ይህ አውቶሜትድ የውጤት ተኮር ምዘና ሲስተም የማዕከሉን፣ በማዕከሉ ውስጥ የሚገኙ የስራ ሂደቶችን፣ የቡድን መሪዎችና ግለሰቦች ስራዎቻቸውን የሚያቅዱበት፣ አፈፃፀማቸውን የሚመዘግቡበትና የአፈፃፀም ምዘና ሪፖርት ማግኘት የሚችሉበት ያለምንም ሰው ጣልቃ ገብነት በኮምፒውተር አማካኝነት የሚከወን የተማከለ ሲስተም ነው። ቴክኖሎጂ ትንተናና ትንበያ በሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል ስር ከሚገኙት ዋና ዋና የስራ ሂደቶች ዉስጥ አንዱ ሲሆን በዋነኝነት ቴክኖሎጂዎችን ከማህበረ-ኢኮኖሚያዊ፣ ከባህል፣ ከዝግጁነት፣ ከአካባቢ፣ ከስጋት፣ ወደፊት ከሚያስከትሉት ተፅዕኖ እና ከሌሎች ዕይታዎች አንፃር በማየት ላይ ትኩረት ያደርጋል። የቴክኖሎጂ ትንተናና ትንበያ ስራን ለማከናወን የተለያዩ ደረጃዎች የሚታለፉ ሲሆን መረጃ ማሰባሰብ፣ መለየት፣ የቴክኖሎጂዎችን ቅድመ ትንተናና ትንበያ መረዳት እና የማጠቃለያ ሃሳብ ማስቀመጥ ከደረጃዎቹ መሀከል የሚገኙ ናቸው። ከትንተናና ትንበያ የሚገኘው መረጃ ለፖሊሲ አርቃቂዎች፣ ተመራማሪዎች፣ የፈጠራ ባለሙያዎችና ልዩ በሆኑ ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመረጃ ምንጭነት ያገለግላል። ኢሳይንስ በእያንዳንዱ የሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ገፅታ ላይ ትልቅ ሚና የሚጫወት መስክ ነው። ለማንኛውም አይነት ፈር ቀዳጅ ለሆኑ ሳይንሳዊ ጥናቶችና ግኝቶች ከመጀመሪያ ፅንሰ ሃሳብ ጀምሮ የተለያዩ በስርዓት የተቀረፁ ሙከራዎችን ለማካሄድ፣ መረጃዎችን በስርዓት ለመሰብሰብ እንዲሁም ተጓዳኝ የሆኑ መረጃዎችን ለመተንተን የሚያገለግል አስቻይ መሳሪያ ነው። ማንኛውም አይነት የሳይንሳዊ ፅንሰ ሃሳብም ሆነ መላምት ፍላጎት መጠነ ሰፊ የሆነ መረጃ መሰብሰብ መቻል አለበት። ይህንንም ለማጎልበትና ለማሳካት የሚያግዙ ሲስተሞችን ባደጉ የኮምፒውቲንግ ስርዓቶች ለመደገፍ ኢሳይንስ ትልቅ አስተዋፅዖ ይኖረዋል። ኢሳይንስ ሳይንቲስቶች የስራቸውን ውጤት ለማከማቸት፣ ለማብራራት፣ ለመተንተን፣ የግንኙነት አውታራቸውን ለመዘርጋት እንዲሁም የራሳቸውን መረጃ ለሌላ ተመሳሳይ ቡድን ለማካፈል የሚያስችል አሰራርና ሂደትን በውስጡ ያዘለ ነው። የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል የመረጃ ማዕከል እንደ መሆኑ ኢሳይንስን ተግባራዊ ማድረጉ የመረጃ የመሰብሰብና ማሰራጨት ስራዎች በዋናነት ለማቀላጠፍ ያስችላል። እንዲሁም የመረጃ ማዕከሉ በውስጡ የምርምር ስራዎችን የሚሰራ ስለሆነ የምርምር ስራዎችን በተሻለ ጥራትና አቅም እንዲሰሩ ኢሳይንስ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለው። ከሳ.ቴ.መ.ማ. ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት • የኮሪያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንፎርሜሽን ተቋም • የቻይና ሳይንሳዊና ቴክኒካል ኢንፎርሜሽን ተቋም • የማሌዢያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንፎርሜሽን ተቋም • የፊሊፒንስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንፎርሜሽን ተቋም የኢትዮጵያ ድርጅቶች የኢትዮጵያ መንግሥት የመረጃና የመገናኛ ቴክኖዎሎጂ
47692
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8A%A9%E1%88%AA%20%E1%8A%A0%E1%89%B0%E1%88%AD
አኩሪ አተር
አኩሪ አተር () የአባዝርት አትክልት ዝርያ ነው። በየጊዜው አኩሪ አተርን መመገብ ለሴቶች ጉዳት ባያደርግም፣ ለወንዶች ጤናማ እንደማይሆን በሰፊ ቢታወቅም በአንዳንድ አገር ባሕል አመጋገብ በብዛት ይጨመራል። ከ20ኛዉ ክፍለ ዘመን አንስቶ በተለይ አሜሪካን ዉስጥ ወርቃማዉ ወይም ተዓምረኛዉ እህል የሚል ስያሜ አግኝቷል። አኩሪ አተር በፕሮቲን እና ቅባት ምንጭነቱ የሚወዳደረዉ የእህል ዘር የለም። ባለሙያ ካገኘም ለመጠጣትም ለመበላትም የሚችል የእህል ዘር ነዉ። ስለአኩሪ አተር ሲወሳ ብዙዎች የሚያስታዉሱት ለሕፃናት አካል ግንባታ ጠቃሚ መሆኑ ብዙ ጊዜ የተነገረለትን የአኩሪ አተር ወተት ሊሆን ይችላል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በኢትዮጵያዉያን የምግብ ጣዕም ለዛ ተላብሶ በተለያየ ምግብነት መቅረብ እንደሚችል እየታየ ነዉ። አኩሪ አተር ወደኢትዮጵያ የገባዉ በ1950ዎቹ መሆኑን ነዉ በእህሉ ላይ ምርምር የሚያደርጉት ባለሙያዎች የሚያስረዱት። በአኩሪ አተር ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተደረገዉ ዝርያ የማዉጣት ምርምርም 22 ዓይነት ዘሮች እስካሁን ተገኝተዋል። በኢትዮጵያ የአኩሪ አተር ብሔራዊ ምርምር ፕሮጀክት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ትዕዛዙ ደጉ ስድስት ዘርፎች ያሉት የምርምር ፕሮጀክት እህሎቹን እርስ በርስ በማዳቀል የሚፈለገዉን የጥራት ደረጃ እንዲይዝ ማድረግ፤ ምርትና በሽታ መቋቋም ላይ ያተኮረ ምርምርም ያካሂዳል። አኩሪ አተርን በሀገር ዉስጥ በ12 የምርምር ማዕከላት ላይ ከፍተኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ፤ መካከለኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ እና ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ምርምሩ ይካሄዳል። ምርምሩ በዚህ አያበቃም ሰብል ክብካቤን በሚመለከት መቼ መዘራት አለበት የሚለዉ እና የአመራረት ሥርዓት ማለትም አኩሪ አተር ከየትኛዉ እህል ጋር ተፈራርቆ ይዘራ፤ ከየትኛዉስ ጋር ተሰባጥሮ ይዘራ የሚለዉ ጥናትም የፕሮጀክቱ አንድ አካል ነዉ። አኩሪ አተርን ሰብልን ሊያጠቁ የሚችሉ አረም ሆነ ተባይ ወይም በሽታ የቱ እንደሆነም ክትትል ይደረጋል። ስለአኩሪ አተር ጥቅም የሚዘረዝሩ ዘገባዎች የመኖራቸዉን ያህል በተፈላጊነቱ ምክንያት በተለይ ደቡብ አሜሪካ ዉስጥ ደኖች እንዲጨፈጨፉ ምክንያት ሆኖ በሥነምህዳሩ ላይ ጫና እስካተለ የሚያወሱም አሉ። አኩሪ አተር ሀገር ዉስጥ በከፍተኛ ደረጃ የሚመረተዉ በቤንሻንጉል ጉምዝ እና በኦሮሚያ ክልል ነዉ። አኩሪ አተርን በብዛት ከሚያመርቱ ሃገራት ዩናትድ ስቴትስ፤ ብራዚል እና አርጀንቲና ቀዳሚዎቹ ናቸዉ። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ተቋም በአኩሪ አተር ላይ አመራረትም ሆነ ምግብ ዝግጅት ላይ ምርምር ሲያካሂድ የቆየ መሆኑን የገለፁት በግብርና ምርምር ተቋሙ የምግብ ሳይንስ ተመራማሪ እና የብሔራዊ አስተባባሪ አቶ ቢላቱ አግዛ አኩሪ አተር በኢትዮጵያ በምግብነት ያን ያህል አልተለመደም ይላሉ። ከአኩሪ አተር የተቀላቀለበት ኬክ ከአኩሪ አተር ወተት ለማዘጋጀት ሲታሰብ እህሉን ከአንድ ቀን በፊት ለቅሞና አጥቦ ለ15 ደቂቃ ያህል መቀቀል ያስፈልጋል። ከዚያም አዉጥቶ ተዘፍዝፎ ያድራል። ከዚያም የራሰዉን አኩሪ አተር ልጣጩን በሚገባ በዉኃ አስለቅቆ በትንሽ በትንሹ እየቆነጠሩ ፈጭቶ እንደእህሉ መጠን ዉኃ ጨምሮ መቀቀልና መጭመቅ ነዉ። እንደባለሙያዉ ከሆነም ለአንድ ኪሎ አኩሪ አተር ስምንት ሊትር ዉኃ ያስፈልጋል። ተፈጥሮን ተከትሎ የማይበቅል እህልም ሆነ በተፈጥሮ ሥርዓት ያላደጉ እንስሳትን መመገብ ለጤና አደገኛ መሆኑን በተግባር የተረዳዉ ምዕራቡ ዓለም በአሁኑ ጊዜ ፊቱን ከእንስሳት ተዋፅኦ ወደተክሎችና ሰብሎች አዙሯል። በዚህ ምክንያትም ከአኩሪ አተር የሚገኙ የምግብ ተዋፅኦዎች ተመራጭነትን እያገኙ ነዉ። ከአኩሪ አተር ወተት እና አይቡ እንደሚገኝ ሁሉ የአኩሪ አተር ሥጋም አለዉ። የአኩሪ አተር አይብ በአኩሪ አተር ዘር እና አመራረት ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ ምርምር ሲደረግ ረዥም ዓመታት አስቆጥሯል። የምግብ ዝግጅቱን ተመለከተ የሚካሄደዉ ምርምር ብቻም አስር ዓመታት እንደቆየ አቶ ቢላቱ ገልጸዋል። የግብርና ምርምር ተቋሙ የአኩሪ አተርን ምግብነት ለማላመድ በጀመረዉ እንቅስቃሴ ለአምራቹቹ ብቻ የምግብ ዝግጅት ሥልጠና ከመስጠት የተቋሙ ሠራተኞችም አዉቀዉት ሙያዉን በማስፋፋት በኩል አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ በሚል አሰልጥኗል። አቶ ቢላቱ እንደገለፁልን ኢትዮጵያ አኩሪ አተርን ብታመርትም ለዉጭ ገበያ ነዉ። በአንፃሩ የተዘጋጁትን የአኩሪ አተር ምርቶች ወደሀገር ታስገባለች። ከዚህም ሌላ በተለያዩ አካላት የአኩሪ አተር ምግብ አዘገጃጀትን የማስተዋወቁ ሥራ እንደሚከናወን ያመለከቱት የምግብ ምርምር ባለሙያ ይህ ወጥነት እንዲኖረዉ እየተሠራ መሆኑንም ሳይገልፁ አላለፉም። አኩሪ አተር ላይ የሚደረገዉ ምርምርም ሆነ የምግብ አዘገጃጀቱ ጥናት ዋና ዓላማ እህሉ ሀገር ዉስጥ ጥቅሙ ታዉቆ ኅብረተሰቡ ከሚገዙ ምርቶቹ ይልቅ በየቤቱ በቀላሉ ማዘጋጀቱን ለምዶ እንዲጠቀምበት ማድረግ እንደሆነ ነዉ ባለሙያዎቹ ያስረዱት። በተጨማሪም ከዉጭ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለም አመልክተዋል።
15910
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8C%82%E1%8A%A6%E1%88%9C%E1%89%B5%E1%88%AA%E1%8A%AD%20%E1%8B%9D%E1%88%AD%E1%8B%9D%E1%88%AD
የጂኦሜትሪክ ዝርዝር
በሒሳብ ጥናት ውስጥ አንድ የቁጥሮች ዝርዝር በቀዳሚና ተከታይ አባሎቹ መካከል ቋሚ ውድር () ካለው ያ ዝርዝር የጆሜትሪ ዝርዝር ይባላል። ምሳሌ ፦ እያንዳንዱን ቀጣይ ቁጥር ከፊት ያለውን ቁጥር በ1/2 ኛ በማባዛት ማግኘት ስለምንችል ከላይ የተቀመጡው ዝርዝር የጆሜትሪ ዝርዝር ይባላል። የጆሜትሪ ዝርዝር ቀላል ቢመስልም ጥቅሙ ግን ስፋት ባላቸው የጥናትና ምርት ምህንድስና ስራወች ላይ ከፍተኛ ጠቃሚነት አለው። አንድናንድ የጆሜትር ድርድሮች ለዘላለም ይቀጥሉ እንጂ ድምር ውጤታቸው ግን የተወሰነ ቋሚ ቁጥር ስለሆነ ለካልኩለስ ጥናት መወለድ እና እድገት ከፍተኛ አስተዋጾ አድርጓል። ባጠቃላይ መልኩ የጆሜትሪ ዝርዝር በምህንድስና፣ ስነ-ተፈጥሮ፣ ካልኩለስ፣ ሒሳብ፣ ስነ-ህይወት፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ፣ ስነ-ንዋይ] እና መሰል የጥናት ዘርፎች ውስጥ ግልጋሎት እየሰጠ ያለ የሒሳብ መሳሪያ ነው። የጋራ ውድር ከላይ እንዳየነው እያንዳንዱ የጆሜትሪ ዝርዝር አባል ከፊት ካለው አባል በአንድ ቋሚ ቁጥር እይተባዛ የሚገኝ ነው። እታች ያለው ሰንጠረዥ ይሄን ጉዳይ ለማስረዳት ይሞክራል፦ እያንዳንዱ አባል ቁጥር ባህርይ እንግዲህ በውድሩ መጠን ይወሰናል: ውድሩ በ-1 እና በ+1 መካከል ከሆነ፣ የድርድሩ አባሎች ቁጥራቸው በጨመረ ጊዜ ይዘታቸው እየተመናመነ እና እየከሱ ይሄዳሉ፣ በዚህ ምክንያት ወደ ዜሮ በማያቋርጥ ሁኔታ ይነጉዳሉ። ከላይ ውድሩ 1/2ኛ የሆነው ዝርዝር አባላቱ ወደ ዜሮ እየተጠጉ እንደሚሄዱ በአይነ ህሊናችን ልንደርስበት እንችላለን :፡ ወደሁዋላ ላይ እንደምናየው ይህ ጸባይ፣ አጠቃላይ ድምራቸው ቋሚ ቁጥር እንዲሆን አስችሏቸዋል። በአንጻሩ የድርድሩ ውድር ከ -1 ካነሰ ወይም ከ1 ከበለጠ፣ የድርድሩ አባሎች እየወፈሩና መጠን እያጡ ይሄዳሉ። እነዚህ አባሎች ቢደመሩ፣ ባይነ ህሊናችን ማስተዋል እንድምንችለው ድምሩ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ እንጂ እያነሰ አይሄድም። በዚህም ክንያት ማንንም የማይጠጋ ዝርዝር () እንለዋለን። ውድሩ +1 ከሆነ አባል ቁጥሮቹ አንድ ቋሚ ቁጥር ይይዛሉ። ለምሳሌ የመጀመሪያው ቁጥር 2 ከሆነ፣ ድርድሩ እንግዲህ 2፣2፣2፣2፣2፣2፣2፣2... ይሆናል ማለት ነው። የዚህ ዝርዝር ድምር ወጤትም እያደገ ስለሚሄድ ማንንም ቁጥር አይጠጋም ስለዚህ ማንንም የማይጠጋ ዝርዝር ነው ማለት ነው። በአንጻሩ ውድሩ -1 ክሆነ አባል ቁጥሮቹ አንድ አይነት መጠን ኖሮዋቸው ነገር ግን በነጌትቭ እና ፖዘቲቭ ቁጥርነት ይዋልላሉ። ለምሳሌ የመጀመሪያው ቁጥር -3 ቢሆን ድርድሩ ይህን ይመስላል -3፣3፣-3፣3፣-3፣... የዚህ ዝርዝር ውጤትም 0፣ -3፣ 0፣ -3፣...እያለ ዥዋዥዌ ስለሚጫወት፣ ማንንም የማይጠጋ ዝርዝር ነው ማለት ነው። የጆሜትሪ ዝርዝር ድምር ውጤት ሊተነበይ ይችላል። ይህ ግን እሚሆነው ወይም ለተወሰኑ የዝርዝር አባሎች ወይም ደግሞ ለየተይሌሌ ከሆነ ውድራቸው በ-1 እና በ1 መካከል ለሆኑት ወይም ደግሞ በሌላ አባባል አባል ቁጥራቸው ወደ ዜሮ እየተጠጋ ለሚሄዱት ብቻ ነው። ድምሩም የሚገኝበት ዘዴ በጣም ቀላል ነው ምክንያቱም እያንዳንዱ አባል ከሱ በፊት ያለው አባል ብዜት ስለሆነና ማብዣውም ቋሚ ስለሆነ ይህን ተመሳሳይ ባህርይ የማስላቱን መንገድ እጅግ ቀላል ያድረገዋል። ይህን ዘዴ እንመልከት፦ የሚከተለውን የጆሜትሪ ዝርዝር ድምር እንመልከት: የዚህ ዝርዝር ውድር እንግዴህ 2/3ኛ ነው። እንግዲህ ድርድሩን በሙሉ በ2/3ኛ ብናበዛ, ድሮ 1 የነበር አሁን 2/3ኛ ይሆናል, 2/3 ድግሞ 4/9 ይሆናል, 4/9 ወደ 8/27ኛ ይለወጣል ...ወዘተረፈ የመጀመሪያው ቁጥር 1 በ 2/3ኛ ከመለወጡ ውጭ፣ ይህ አዲሱ ዝርዝር ከድሮው ዝርዝር ጋር ምንም ልዩነት የለውም ። እንግዴህ አዲሱን ዝርዝር ከድሮው ዝርዝር ስንቀንስ ከመጀመሪያው አባል በቀር የተቀሩት አባሎች በሙሉ እርስ በርሳቸው ይጠፋፋሉ: በዚህ መንገድ ማናቸውንም ከራሳቸው ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ድምሮችን መደመርና ውጤቱን ማወቅ እንችልለን። አጠቃላይ ፎርሙላ ወደራቸው 1 ወይም -1 የሆኑ የጆሜትሪ ድርድሮች የመጀመሪያ በ+1 አባሎች ድምር ውጤት ይህን ይመስላል: እዚ ላይ ማለት የድርድሩ የመጀመሪያ አባል ማለት ነው, ደግሞ የጋራው ውደር ነው። ይህን ፎርሙላ ለማግኘት በሚከተለው መንገድ እንንቀሳቀሳለን: ከላይ 'ን ለጊዜው ገለል አድርገን በ 1 ስለተካናት የላይኛው ፎርሙላ አጠቃላይ መሆኑ ቀርቶ የመጀመሪያው ቁጥራቸው 1 ለሆኑ ድርድሮች ብቻ ይሰራል ማለት ነው። አጠቃላይ ለማድረግ እንግዲ ሁሉንም በ' ማብዛት ግድ ይላል። ከላይ ያለው ፎርሙላ እንግዲ የሚሰራው ውድራቸው 1 ላልሆኑ ለማናቸውም የጆሜትሪ ዝርዝር ሲሆን፣ የተደማሪወቹ ቁጥር የተወሰነ ወይም ደግሞ የትየለሌ ያልሆነ መሆን አለበት። ውድራቸው በ-1 እና በ 1ለሆኑ ድርድሮች ግን፣ አባሎቻቸው ማለቂያ ባይኖራቸው እንኳ ድምራቸው ይገኛል። ከዚህ በታች ዘዴው ተዘርዝሯል፦ በሚሆን ጊዜ፣ ከላይ የተጻፈው ፎርሙላ የሚከተለውን መልክ ይይዛል፦ ይህ ፎርሙላ የተገኘበትም መንገድ ይህን ይመስላል፦ አጠቃላዩ ፎርሙላን ለማግኘት እንግዲህ በ ማብዛት ሊኖርብን ነው ማለት ነው። ይህ ፎርሙላ የሚሰራው ለተጠጊ ድርድሮች ብቻ እንደሆነ እንዳንረሳ። ማለት ተጠጊ ያልሆኑ ድርድሮችን በደፈናው ከላይ በተቀመጠው ፎርሙላ መደመር ይቻላል፦ ለምሳሌ ውድሩ 10 የሆነ አንድ ዝርዝር በላይ ባለው ፎርሙላ ብንደመርው የሚል መልስ እናገኛልን ነገር ግን ይሄ ስህተት ነው ምክናይቱም ውድሩ 10 የሆነ ዝርዝር ተጠጊ ዝርዝር አይደለማ። ይህ ጥንቃቄ ለ የአቅጣጫ ቁጥሮች ሳይቀር ይሰራል። ለምሳሌ የውድሩ መጠን ከ1 ካነሰ የሚከተለው ዝርዝር ተጠጊ ዝርዝር ይሆናል፦ ሲሆን, ከላይ የጻፍነው ወደዚህ ይቀየራል፦ እስካሁን በቁጥር የጻፍነውን በቅርጻ-ቅርጽ ለማየት የሚከተለውን ምሳሌ ከ 1996 እንውሰድ: ድግግም የነጥብ ቁጥሮችን ዋጋ ለማግኘት እራሳቸውን የሚደጋግሙ የነጥብ ቁጥሮች ውድራቸው የ1/10 ንሴት ()እንደሆነ አድርገን መተርጎም እንችላለን። ለምሳሌ: እንግዲህ ይህን ተደጋጋሚ የነጥብ ቁጥር ወደ ክፋይ ለመለወጥ ከላይ ያገኘናቸውን ፎርሙላወች መጠቀም እንችላለን: ይህ ፎርሙላ ለምትደጋገም አንዲት ቁጥር ብቻ ሳይሆን በቡድን ሆነው ለሚደጋገሙ ቁጥሮች ሳይቀር ይሰራል። ምሳሌ: ከዚህ እንደምንረዳው ማናቸውንም ተደጋጋሚ የነጥብ ቁጥሮች በቀላሉ በንደዚህ መንገድ ወደ ክፋይ ቁጥሮች መቀየር እንችላለን፦ የፓራቦላን ስፋት በአርኪሜድ መንገድ ለማግኘት (ያለ ካልኩለስ) አርኪሜድስ የተሰኘው የጥንቱ የግሪክ ሒሳብ ተመራማሪ በፓራቦላና በቀጥታ መስመር መካከል ያለውን ስፋት መጠን በጆሜትሪ ዝርዝር ነበር ያገኘው። በዚህም ጥረቱ አርኪሜድስ የፓራቦላውን አጠቃላይ ስፋት የሰማያዊው ሶስት ማእዘን 4/3ኛ እንደሆነ አረጋግጦአል። ይህ አስደናቂ የሚሆንበት ያለምንም ካልኩለስ ጥናት ይህን ውጤት ማግኘቱ ነው። ማሳመኛ፦ አርኪሜድስ ባደረገው ጥናት እያንዳንዱ ቢጫ ሶስት ማእዘን 1/8 የሰማያዊ ሶስት ማእዘኖችን የስፋት ይዘት እንዳላቸው ተረዳ፣ በተራቸው አረንጓዴወቹ ደግሞ 1/8 የቢጫወቹ እንደሆነ አረጋጠ...ወዘተረፈ.. እንግዲህ ሰማያዊው ሶስት ማእዘን ስፋቱ 1 ካሬ ሜትር ነው ብንል፣ ቢጫውን፣ አረንጌዴውንና ሌሎቹ የትየለሌ በፓራቦላውና በቀሩት ሶስት ማእዘኖች መካከል ያሉትን ጥቃቅን ሶስት ማእዘኖችን ስፋት ለመደመር እንዲህ እናደርጋለን ማለት ነው፦ ከላይ፣ የመጀመሪያው ቁጥር የሚያሳየው የሰማያዊውን ሶስት ማእዘን ስፋት ነው፣ ከዚያ የቢጫ ሶስት ማእዘኖችን፣ ከዚያ የአረንጓዴወቹን፣ ይቀጥላል..። ክፍልፋዮቹን ስናቃልል ይህን እናገኛለን፦ እንደምንገነዘበው ይ ሄ እንግዲህ የጆሜትሪ ዝርዝር ሲሆን የጋራ ውድሩም ነው። ስለዚህ ከላይ ባገኘነው ፎርሙላ መሰረት አጠቃላይ ስፋቱ እንዲህ ይሆናል፦ ድምሩ እንግዲህ ማሳመኑ ተጠናቀቀ ባሁኑ ጊዜ የፓራቦላ ስፋት በ ካልኩለስ ሲጠና፣ የሚገኝበትም ዘዴ የተወሰነ ኢንቴግራል ይባላል። የፍራክታል ጆሜትሪ የጥንቱ ግሪካዊ ዜኖ እንቆቅልሽ ጥንታዊው ዜኖ እንዲህ ሚል እንቆቅልሽ ነበረው- እያንዳንዱን እርምጃ ለመውሰድ መጀመሪያ ግማሹን መንገድ መጓዝ ይጠይቃል፣ ግማሹን ለመጉዋዝ ደግሞ የዚያን ግማሽ መጓዝ ይጠይቃል ወዘተረፈ.... አንድን የተወሰነ ርቀት ለመጓዝ የትየለሌ ርምጃ ስለሚያስፈልግ በዚህ ምክንያት እንቅስቃሴ ባጠቃላይ የማይቻል ነው ይል ነበር። ነገር ግን ከላይ እንዳይነው 1+ 1/2 + 1/4 + 1/8 + ...መልሱ የትየለሌ ሳይሆን አንድ ቋሚ ቁጥር ነው።ማለት ዜኖ ያሰበው የትይለሌ የሚሆኑ የተወሰኑ እርምጃወች ሲደመሩ የተወሰነ ርቀት ሳይሆን የትየለሌ ይሆናል ብሎ ነበር። በዚህ ገጽ መግቢያ ላይ ይህ አስተያየት ስህተት መሆኑን ስላየን፣ የሱ እንቆቅልሽ በዚህ መንገድ ተፈቷል። ስነ ንዋይ ለምሳሌ ሎተሪ ቆርጠው ሽልማቱ 100 ብር ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ በየዓምቱ እስከ እለተ ህልፈትዎ የሚያስከፍል ይሁን። የዛሬ አንድ አመት 100 ብር መከፈልና አሁን 100 ብር በኪስዎ መያዝ አንድ አይደሉም ምክንያቱም አሁን ብሩን ቢያገኙት ስራ ላይ አውለውት ትርፍ ሊያስገኝለወት ይችላልና። የዛሬ ዓመት የሚከፈለው 100 ብር በአሁን ጊዜ ይህን አይነት ዋጋ ለእርስዎ አለው $100 / (1 + እንግዲህ ወለድ ነው. በተመሳሳይ የዛሬ ሁለት ዓመት የሚከፈልዎ $100 አሁን ይህን አይነት ዋጋ ለእርስዎ አለው ፦ $100 / 2 በ2 ከፍ ያለበት ምክንያት ወለዱን ሁለት ጊዜ ሊያገኙ ይችሉ ስለነበር ነው ። ስለዚህ እስከ ዘላለም 100 ብር ቢከፈልዎ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ፣ አሁን ለእርስዎ ያለው ዋጋ ይህን ይመስላል፦ ይህ እንግዲህ የጆሜትሪ ዝርዝር ሲሆን የጋራ ውድሩም 1 / ነው። ከላይ ባገኘነው ፎርሙላ ስንደምረው ለምሳሌ የአመቱ ወለድ 10% ቢሆን , አጠቃላይ ድምሩ $1000 ነው ማለት ነው። ማለት ዘላለምወን 100$ በየዓመቱ ቢከፈልወና አሁን 1000 ብር ኪስወ ቢኖር ሁለቱ አንድ ዋጋ ነው ያላቸው ( እዚህ ላይ ማወቅ ያለብን 100 ብሩን ስራ ላይ አውለወት በአመት 10% ወለድ እየወለደልወ እንደሆነ ነው)። ይህ አይነት ስሌት ለ ሞርጌጅ ክፍያ በባንኮች ዘንድ የሚጠቀሙበት ነው። የስቶክ ተጠባቂ ዋጋንም ካሁኑ ለመተንበይ ይጠቅማል። ባጠቃላይ የብድርን አመታዊ ወለድ ፐርሰንቴጅ ለማስላት ነጋዴወችና ባንኮች የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው። የታወቁ አንዳንድ የጆሜትሪ ድርድሮች የጋንዲ ዝርዝር 1/2 + 1/4 + 1/8 + .....= 1 እንደሆነ የሚያሳይ ምሳሌ፦ የዚህ ክፍል ታሪክና ፍልስፍና የኮምፒዩተር ሳይንስ ተጨማሪ ድረ ገጾች ኤሌክትሪካል ኢንጂኔሪንግ መደብ :ሥነ ቁጥር
52821
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8A%AD%E1%88%B1%E1%88%9D%20%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%A5%E1%89%B5
አክሱም መንግሥት
የአክሱም መንግሥት (ኤርትሪያ) መንግሥተ አክሱም (ግዕዝ) በ1ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ–ሐ. በ960 ዓ.ም የአክሱም ወይም የአክሱም ንጉስ ኢንዱቢስን የሚያሳይ የአክሱማይት ገንዘብ ንጉሥ የሚያሳይ ምንዛሬ የአክሱም መንግሥት በከፍተኛ ደረጃ በ6ኛው ክፍለ ዘመን የአክሱም መንግሥት በከፍተኛ ደረጃ በ6ኛው ክፍለ ዘመን ካፒታል ኤርትራ አክሱም ኩባር/ጃርማ (ከ800 ዓ.ም. በኋላ) የተለመዱ ቋንቋዎች (ከ1ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ) ክርስትና (ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፤ ከ4ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በኋላ በይፋ) አክሱማይት አምልኮተ አምልኮ (ከ350 በፊት ይፋ የሆነ) የአጋንንት ስም(ዎች) አክሱማይት፣ ኢትዮጵያዊ፣ አቢሲኒያ የመንግስት ንጉሳዊ አገዛዝ • ሐ. 100 ዛ ሃቃላ (በመጀመሪያ የታወቀው) • ሐ. 940 ዲል ናኦድ (የመጨረሻ) ታሪካዊ ዘመን ክላሲካል ጥንታዊነት እስከ መጀመሪያው የመካከለኛው ዘመን • የተቋቋመ በ 1 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ • ቀደምት የደቡብ አረቢያ ተሳትፎ 3 ኛው ክፍለ ዘመን • የሜሮን ድል • የኢዛና ወደ ክርስትና መቀየሩ • የሂሚያራይት መንግሥት ወረራ • ቀደምት የሙስሊም ወረራዎች 7 ኛው ክፍለ ዘመን • በንግስት ጉዲት ተደምስሷል ሐ. በ960 ዓ.ም 1,250,000 ኪሜ2 (480,000 ካሬ ማይል) ምንዛሬ ምንዛሬ የቀደመው በ ተሳክቷል። የዛግዌ ሥርወ መንግሥት የሲሚን መንግሥት የሸዋ ሱልጣኔት ዛሬ በከፊል የአክሱም መንግሥት (ግእዝ፡ መንግሥተ አክሱም፣ )፣ እንዲሁም የአክሱም መንግሥት ወይም የአክሱም ኢምፓየር በመባል የሚታወቀው፣ በሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ እና በደቡብ አረቢያ ላይ ያተኮረ መንግሥት ከጥንት ጀምሮ እስከ መካከለኛው ዘመን መጀመሪያ ድረስ ያለ መንግሥት ነበር። የአሁኗ ኤርትራን፣ ሰሜናዊ ጅቡቲን እና ምስራቃዊ ሱዳንን የሚሸፍን ሲሆን በንጉሥ ካሌብ ዘመነ መንግስት ወደ ደቡብ አረቢያ አብዛኛው ክፍል ዘልቋል። አክሱም ለብዙ መቶ ዘመናት የመንግሥቱ ዋና ከተማ ሆና ስታገለግል በ9ኛው ክፍለ ዘመን ግን የንግድ ትስስር በመቀነሱ እና በተደጋጋሚ የውጭ ወረራ ምክንያት ወደ ጃርማ ተዛወረ። ከቀደምት የዲኤምቲ ስልጣኔ በመነሳት መንግስቱ የተመሰረተው በ1ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ሳይሆን አይቀርም። የቅድመ-አክሱማዊ ባህል በከፊል የዳበረው ​​በደቡብ አረቢያ ተጽዕኖ ምክንያት ነው፣ በጥንቷ ደቡብ አረቢያ ስክሪፕት አጠቃቀም እና በጥንታዊ ሴማዊ ሀይማኖት ልምምዶች ላይ ይታያል። ነገር ግን የግእዝ ፊደል በ4ኛው ክፍለ ዘመን ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን መንግሥቱ በሮም እና በህንድ መካከል ባለው የንግድ መስመር ላይ ዋና ኃይል እየሆነ ሲመጣ ወደ ግሪኮ-ሮማን የባህል ሉል በመግባት ግሪክን እንደ ቋንቋ መጠቀም ጀመረ። የአክሱም መንግሥት በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ በአክሱም ኢዛና ሥር ክርስትናን የመንግሥት ሃይማኖት አድርጎ የወሰደው በዚህ ነው። አክሱማውያን ወደ ክርስትና መምጣታቸውን ተከትሎ የሃውልት ግንባታ አቆሙ። የአክሱም መንግሥት በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከነበሩት አራት ታላላቅ ኃያላን መንግስታት ከፋርስ፣ ሮም እና ቻይና ጋር በመሆን በፋርስ ነቢይ ማኒ ነበር። ከኢንዱቢስ የግዛት ዘመን ጀምሮ አክሱም እስከ ቂሳርያ እና ደቡባዊ ህንድ ባሉ ቦታዎች የተቆፈሩትን የራሱን ሳንቲሞች ያወጣል። ግዛቱ በጥንት ዘመን መስፋፋቱን ቀጠለ፣ ሜሮንን በመቆጣጠር በጣም አጭር ጊዜ ወሰደ፣ ከርሱም "ኢትዮጵያ" የሚለውን የግሪክ አገላለጽ የወረሰ ነው። የአክሱማውያን የቀይ ባህር የበላይነት ያበቃው በአክሱም ካሌብ ዘመነ መንግስት ሲሆን በባይዛንታይን ንጉሠ ነገሥት ጀስቲን ቀዳማዊ ትዕዛዝ የአይሁድ ንጉሥ በዱ ኑዋስ በክርስቲያኖች ላይ እየደረሰ ያለውን ስደት ለማስቆም በየመን የሚገኘውን የሂሚያራይት መንግሥት ወረረ። ከሂያር ጋር በመቀላቀል፣ የአክሱም መንግሥት በግዛቱ ትልቁ ነበር። ሆኖም ግዛቱ በአክሱማይት-ፋርስ ጦርነቶች ጠፍቷል። የመንግሥቱ አዝጋሚ ማሽቆልቆል የጀመረው በ7ኛው ክፍለ ዘመን ነው፣ በዚህ ጊዜ ምንዛሪ ማውጣት አቆመ። የፋርስ (በኋላም ሙስሊሞች) በቀይ ባህር ውስጥ መገኘታቸው አክሱምን በኢኮኖሚ እንዲሰቃይ አድርጓቸዋል፣ እናም የአክሱም ከተማ ነዋሪ ቁጥር ቀንሷል። ከአካባቢያዊ እና ውስጣዊ ሁኔታዎች ጎን ለጎን, ይህ የመቀነስ ምክንያት ነው. የአክሱም የመጨረሻዎቹ ሶስት መቶ ዘመናት እንደ ጨለማ ዘመን ተቆጥረዋል፣ እናም እርግጠኛ ባልሆኑ ሁኔታዎች መንግስቱ በ960 አካባቢ ፈራረሰ። በጥንት ዘመን ከነበሩት ዋና ዋና ግዛቶች መካከል አንዱ ቢሆንም፣ የአክሱም መንግሥት በመካከለኛው ዘመን ሁሉ ኢትዮጵያ ተገልላ በነበረችበት ጊዜ ጨለማ ውስጥ ወደቀች። ሀ የኢዛና ድንጋይ ኢዛና ወደ ክርስትና መግባቱን እና ሜሮንን ጨምሮ በአካባቢው ያሉትን የተለያዩ ህዝቦች መገዛቱን መዝግቧል። አክሱማዊት መንህር በባላው ካላው (መተራ) ሰናፌ አቅራቢያ የአክሱም መንግሥት በኤርትራና የሚገኝ የንግድ ግዛት ነበር። ከ100-940 ዓ.ም ገደማ ነበረ፣ ከአይረን ዘመን ፕሮቶ-አክሱማይት ዘመን ሐ. ከክርስቶስ ልደት በፊት በአራተኛው ክፍለ ዘመን ታዋቂነትን ለማግኘት በአንደኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም. በአክሱም መጽሃፍ መሰረት የግዛቱ የመጀመሪያ ዋና ከተማ ማዛብር የኩሽ ልጅ ኢቲዮጲስ ነው የተሰራችው ዋና ከተማዋ በኋላ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ወደ አክሱም ተዛወረች። መንግሥቱ በአራተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ "ኢትዮጵያ" የሚለውን ስም ይጠቀም ነበር. የአክሱም ኢምፓየር በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛዎቹ የኤርትራ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ፣ በምእራብ የመን - የግብፅን ጀልባ ዲዛይን በመጠቀም የወረረውን - እና አንዳንድ የምስራቅ ሱዳን ክፍሎች ይስፋፋ ነበር። የግዛቱ ዋና ከተማ አሁን በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኝ አክሱም ነበረች። ዛሬ ትንሽ ማህበረሰብ፣ አክሱም ከተማ በአንድ ወቅት የተጨናነቀች ዋና ከተማ፣ የባህል እና የኢኮኖሚ ማዕከል ነበረች። ሁለት ኮረብታዎች እና ሁለት ጅረቶች በከተማይቱ ምስራቅ እና ምዕራብ ይገኛሉ; ምናልባት ይህንን አካባቢ ለማስተካከል የመነሻ ተነሳሽነት ሊሆን ይችላል። ከከተማው ውጭ ባሉት ኮረብታዎች እና ሜዳዎች ላይ የአክሱማውያን መቃብር ስቴሊ ወይም ሐውልት የሚባሉ የተንቆጠቆጡ የመቃብር ድንጋዮች ነበሯቸው። ሌሎች ጠቃሚ ከተሞች የሃ፣ ሃውልቲ-መላዞ፣ ማታራ፣ አዱሊስ እና ቆሃይቶ፣ የመጨረሻዎቹ ሶስት ከተሞች አሁን በኤርትራ ይገኛሉ። በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በኤንዱቢስ የግዛት ዘመን፣ የራሷን ገንዘብ ማውጣት የጀመረች ሲሆን በማኒ ከሳሳንያን ኢምፓየር፣ ከሮማ ኢምፓየር እና ከቻይና "ሶስት መንግስታት" ጋር በዘመኑ ከነበሩት አራት ታላላቅ ኃያላን መንግስታት አንዱ ተብሎ ተሰየመ። አክሱማውያን በ325 ወይም 328 ዓ.ም በንጉሥ ኢዛና ክርስትናን እንደ መንግሥታዊ ሃይማኖት የወሰዱ ሲሆን አክሱም የመስቀልን ምስል በሳንቲሞቹ ላይ የተጠቀመች የመጀመሪያዋ ሀገር ነች። በ3ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ (ምናልባትም ከ240-260 ዓ.ም.) አካባቢ፣ በሴምብሮውተስ የሚመሩት አክሱማውያን ሴሴይን አሸነፉ፣ ሴሴያ የአክሱም መንግሥት ገባር ሆነ። በ330 አካባቢ፣ የአክሱም ኢዛና ሠራዊቱን እየመራ ወደ ሜሮ ግዛት በመግባት ከተማዋን ራሷን ወረረች። አንድ ትልቅ የድንጋይ ሐውልት እዚያው ቀርቷል፣ ወረራውም በኢዛና ድንጋይ ላይ የተያያዘ ነው።
53393
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AB%E1%8A%93%E1%89%A2%E1%88%B5%20%28%E1%88%98%E1%8B%B5%E1%88%83%E1%8A%92%E1%89%B5%29
ካናቢስ (መድሃኒት)
ካናቢስ፣ ማሪዋና በመባልም የሚታወቀው ከሌሎች ስሞች መካከል፣ ከካናቢስ ተክል የመጣ የስነ-ልቦና መድሃኒት ነው። የመካከለኛው ወይም የደቡብ እስያ ተወላጅ የሆነው የካናቢስ ተክል ለመዝናኛ እና ለሥነ-ተዋፅኦ ዓላማዎች እና ለተለያዩ ባህላዊ መድሃኒቶች እንደ መድኃኒትነት ለዘመናት ሲያገለግል ቆይቷል። ) የካናቢስ ዋነኛ የስነ-አእምሮ አካል ነው, ይህም በፋብሪካው ውስጥ ከሚገኙት 483 ታዋቂ ውህዶች አንዱ ነው, ቢያንስ 65 ሌሎች ካናቢኖይዶችን ጨምሮ, ለምሳሌ ካናቢዲዮል (ሲቢዲ). ካናቢስ በማጨስ፣ በመተንፈሻነት፣ በምግብ ውስጥ ወይም እንደ ማጭድ መጠቀም ይቻላል። ካናቢስ የተለያዩ አእምሯዊ እና አካላዊ ተፅእኖዎች ያሉት ሲሆን እነዚህም የደስታ ስሜት፣ የአስተሳሰብ ለውጥ እና የጊዜ ስሜት፣ ትኩረት የመሰብሰብ ችግር፣ የአጭር ጊዜ የማስታወስ ችሎታ ችግር፣ የሰውነት እንቅስቃሴ (ሚዛን እና ጥሩ ሳይኮሞተር ቁጥጥር)፣ መዝናናት እና የምግብ ፍላጎት መጨመር ይገኙበታል። ሲጋራ ሲጨስ በደቂቃዎች ውስጥ የተፅዕኖ መጀመሩ ይሰማል፣ ነገር ግን ሲበላ እስከ 90 ደቂቃ ሊወስድ ይችላል። በተጠቀመው መጠን ላይ በመመርኮዝ ውጤቱ ከሁለት እስከ ስድስት ሰአታት ይቆያል. ከፍተኛ መጠን በሚወስዱበት ጊዜ፣ የአዕምሮ ውጤቶቹ ጭንቀትን፣ ማታለልን (የማጣቀሻ ሃሳቦችን ጨምሮ)፣ ቅዠት፣ ፍርሃት፣ ፓራኖያ እና ሳይኮሲስ ሊያካትት ይችላል። በካናቢስ አጠቃቀም እና በሳይኮሲስ ስጋት መካከል ጠንካራ ግንኙነት አለ, ምንም እንኳን የምክንያት አቅጣጫው ክርክር ቢሆንም. አካላዊ ተፅእኖዎች የልብ ምት መጨመር፣ የመተንፈስ ችግር፣ ማቅለሽለሽ እና እናቶቻቸው በእርግዝና ወቅት ካናቢስ በሚጠቀሙ ህጻናት ላይ የባህሪ ችግርን ያጠቃልላል። የአጭር ጊዜ የጎንዮሽ ጉዳቶች የአፍ መድረቅ እና ቀይ አይኖችም ሊያካትት ይችላል። የረዥም ጊዜ የጎንዮሽ ጉዳቶች ሱስን፣ በጉርምስና ዕድሜ ላይ እያሉ አዘውትረው መጠቀም በጀመሩ ሰዎች ላይ የአእምሮ ችሎታ መቀነስ፣ ሥር የሰደደ ሳል፣ ለአተነፋፈስ ኢንፌክሽን ተጋላጭነት እና ካናቢኖይድ ሃይፐርሜሲስ ሲንድሮም ሊያካትት ይችላል። ካናቢስ በአብዛኛው ለመዝናኛ ወይም ለመድኃኒትነት ጥቅም ላይ ይውላል፣ ምንም እንኳን ለመንፈሳዊ ዓላማዎችም ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል። እ.ኤ.አ. በ 2013 ከ128 እስከ 232 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ካናቢስን ተጠቅመዋል (ከ15 እስከ 65 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካሉት የዓለም ሕዝብ ከ2.7 እስከ 4.9%)። በአለም ላይ በብዛት ጥቅም ላይ የሚውለው ህገ-ወጥ መድሃኒት ሲሆን በዛምቢያ፣ ዩናይትድ ስቴትስ፣ ካናዳ እና ናይጄሪያ ውስጥ በአዋቂዎች ዘንድ ከፍተኛ ጥቅም ላይ ይውላል። ከ1970ዎቹ ጀምሮ የሕገ-ወጥ ካናቢስ አቅም ጨምሯል፣ የ ደረጃዎች እየጨመረ እና የ ደረጃዎች እየቀነሱ መጥተዋል። የካናቢስ ተክሎች ቢያንስ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ 3 ኛው ሺህ ዓመት ጀምሮ ይበቅላሉ, መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ቢያንስ ከ 2,500 ዓመታት በፊት በኤሺያ ፓሚር ተራሮች ውስጥ ለሥነ-ልቦናዊ ተፅእኖዎች ሲጨስ ነበር. ከ 14 ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ካናቢስ በህጋዊ እገዳዎች ተጥሏል. ካናቢስ መያዝ፣ መጠቀም እና ማልማት በአብዛኛዎቹ አገሮች ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሕገ-ወጥ ነው። እ.ኤ.አ. በ2013 ኡራጓይ የካናቢስ መዝናኛን ህጋዊ ያደረገች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች። ይህን ለማድረግ ሌሎች አገሮች ካናዳ፣ ጆርጂያ፣ ማልታ፣ ሜክሲኮ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ታይላንድ ናቸው። በዩኤስ ውስጥ፣ መድኃኒቱ በፌዴራል ሕገወጥ ቢሆንም፣ የካናቢስ መዝናኛን መጠቀም በ23 ግዛቶች፣ 3 ግዛቶች እና በዲስትሪክት ኦፍ ኮሎምቢያ ህጋዊ ነው። በአውስትራሊያ ህጋዊ የሆነው በአውስትራሊያ ዋና ከተማ ግዛት ውስጥ ብቻ ነው። ጥቅሞችየህክምና ጥቅሞች የሕክምና ካናቢስ፣ ወይም የሕክምና ማሪዋና፣ በሽታን ለማከም ወይም ምልክቶችን ለማሻሻል ካናቢስ መጠቀምን ያመለክታል። ሆኖም፣ አንድም የተስማማበት ፍቺ የለም (ለምሳሌ፣ ከካናቢስ የተገኙ ካናቢኖይድስ እና ሰው ሠራሽ ካናቢኖይዶች እንዲሁ ጥቅም ላይ ይውላሉ)። ካናቢስ እንደ መድሃኒት የሚደረገው ጥብቅ ሳይንሳዊ ጥናት በምርት ገደቦች እና በብዙ መንግስታት ህገ-ወጥ መድሃኒት ተብሎ በመፈረጁ ተስተጓጉሏል። ካናቢስ በኬሞቴራፒ ወቅት ማቅለሽለሽ እና ማስታወክን ለመቀነስ፣ ኤችአይቪ/ኤድስ ያለባቸውን ሰዎች የምግብ ፍላጎት ለማሻሻል ወይም ሥር የሰደደ ሕመም እና የጡንቻ መወጠርን ለማከም ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚችል የሚጠቁሙ ውሱን መረጃዎች አሉ። ስለ ደህንነት ወይም ውጤታማነት ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ለሌሎች የሕክምና መተግበሪያዎች ጥቅም ላይ የሚውለው ማስረጃ በቂ አይደለም። በኬሞቴራፒ በሚያስከትለው ማቅለሽለሽ እና ማስታወክ፣ በኒውሮፓቲ ሕመም እና በብዙ ስክለሮሲስ ሕክምና ውስጥ ካናቢስ ወይም ተዋጽኦዎችን መጠቀምን የሚደግፉ ማስረጃዎች አሉ። ለኤድስ አባካኝ ሲንድረም፣ ለሚጥል በሽታ፣ ለሩማቶይድ አርትራይተስ እና ለግላኮማ ጥቅም ላይ መዋሉን ዝቅተኛ ማስረጃዎች ይደግፋሉ። እስካሁን ድረስ የካናቢስ የሕክምና አጠቃቀም ህጋዊ የሆነው ካናዳ፣ ቤልጂየም፣ አውስትራሊያ፣ ኔዘርላንድስ፣ ኒውዚላንድ፣ ስፔን እና ብዙ የአሜሪካ ግዛቶችን ጨምሮ በተወሰኑ ግዛቶች ብቻ ነው። ይህ አጠቃቀም ባጠቃላይ የሐኪም ማዘዣ ያስፈልገዋል፣ እና ስርጭቱ ብዙውን ጊዜ የሚካሄደው በአካባቢ ህጎች በተገለጸው ማዕቀፍ ነው። እንደ ዲኤኤ ዋና የአስተዳደር ህግ ዳኛ ፍራንሲስ ያንግ “ካናቢስ በሰው ዘንድ ከሚታወቁት በጣም ደህንነቱ የተጠበቀ የቲራፔቲክ ንቁ ንጥረ ነገሮች አንዱ ነው። 15] የካናቢስ ፍጆታ ሁለቱም ሳይኮአክቲቭ እና ፊዚዮሎጂያዊ ተፅእኖዎች አሉት። "በድንጋይ የተወረወረ" ልምድ በስፋት ሊለያይ ይችላል (ከሌሎች ነገሮች በተጨማሪ) በተጠቃሚው የካናቢስ ቀደምት ልምድ እና ጥቅም ላይ የዋለው የካናቢስ አይነት። 18]: 104 በአመለካከት እና በስሜት ላይ ካለው ተጨባጭ ለውጥ በተጨማሪ በጣም የተለመዱት የአጭር ጊዜ የአካል እና የነርቭ ውጤቶች የልብ ምት መጨመር፣ የምግብ ፍላጎት መጨመር፣ የአጭር ጊዜ እና የስራ ማህደረ ትውስታ መጓደል እና የስነ-አእምሮ ሞተር ቅንጅት ያካትታሉ። የካናቢስ አጠቃቀም ተጨማሪ የሚፈለጉ ውጤቶች ዘና ለማለት፣ አጠቃላይ የንቃተ ህሊና ለውጥ፣ የስሜት ግንዛቤን መጨመር፣ የሊቢዶአቸውን መጨመር እና የጊዜ እና የቦታ ግንዛቤን ማዛባት ያካትታሉ። ከፍ ባለ መጠን፣ ተፅዕኖዎች የተለወጠ የሰውነት ምስል፣ የመስማት እና/ወይም የእይታ ቅዠቶች፣ እና ከ የተመረጠ እክል ሊያካትት ይችላል። ] እና ከስር መሰረዝ. ዋና መጣጥፍ: ካናቢስ ኢንቲዮጂን አጠቃቀም ካናቢስ በበርካታ ሃይማኖቶች ውስጥ የተቀደሰ ደረጃን ይይዛል እና እንደ - በሃይማኖታዊ ፣ ሻማኒክ ወይም መንፈሳዊ አውዶች ውስጥ ጥቅም ላይ የዋለ ኬሚካላዊ ንጥረ ነገር - በህንድ ንዑስ አህጉር ከቬዲክ ዘመን ጀምሮ አገልግሏል። በህንድ ክፍለ አህጉር ውስጥ የካናቢስ ቅዱስ ሁኔታን በተመለከተ በጣም የታወቁት ሪፖርቶች በ1400 ዓክልበ. አካባቢ እንደተፃፈ ከሚገመተው ከአታርቫ ቬዳ የመጡ ናቸው። የሂንዱ አምላክ ሺቫ እንደ ካናቢስ ተጠቃሚ ተገልጿል፣ “የባንግ ጌታ። ፡ በዘመናዊው ባህል የካናቢስ መንፈሳዊ አጠቃቀም በራስተፈሪ እንቅስቃሴ ደቀመዛሙርት በካናቢስ እንደ ቅዱስ ቁርባን እና ለማሰላሰል አጋዥ በሆነ መንገድ ተሰራጭቷል። የመድኃኒት እጽዋት
18358
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8C%BD%E1%88%90%E1%8D%88%20%E1%8B%95%E1%8B%9D%E1%88%AB%20%E1%88%B1%E1%89%B1%E1%8A%A4%E1%88%8D
መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል
መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተከርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ ከብሉይ መጻሕፍት የሚፈረጅ ነው። መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ከዲዩተሮካኖኒካል መጻሕፍት ተቆጥሮ የዕዝራ (ሱቱኤል) ትንቢት ነው። የተጻፈው በዕብራይስጥ ወይም በአራማያ ሲሆን በኋላ (250 አክልበ.) ከ70 ሊቃውንት ብሉይ ኪዳን ጋር ወደ ግሪክ ተተረጎመ፤ ከዚሁም ግሪክ ወደ ሮማይስጥ። እንዲሁም የግዕዝ ትርጉም ከዕብራይስጡ ተሠራ። ከክርስቶስ ስቅለት ውዲህ ግን የአይሁድ ጉባኤ መጽሐፉን ስለ ከለከለው፣ የዕብራይስጥና የግሪክ ትርጉሞች በፍጹም ጠፍተዋል። መጽሐፉ ዛሬው የሚታወቀው ከሮማይስጥ፣ ከግዕዝ፣ ከሶርያ ቋንቋ (ከጥንቱ አራማያ የሚለይ)፣ ከአረብኛና ከአርሜንኛ ትርጉሞች ብቻ ነው። የመጽሐፉ ይዘት እንዲሁ ነው፦ ምዕ. 1፦ ዕዝራ በባቢሎን ምርኮ ላይ አዝኖ ወደ እግዚአብሔር ሲጸለይ፣ ስለ አዳም፣ ኖኅ፣ አብርሃም፣ ዘጸአት፣ ዳዊትና የምርኮው ታሪክ ይተርካል። ባቢሎን በዕውኑ ከጽዮን ይልቅ እንደ ጸደቀች እግዚአብሔርን ይጠይቀዋል፤ ጽዮንን በባቢሎን ስለሚቀጣት፣ ጽዮንም ስትሠቃይ ባቢሎንም ስትደሰት ነውና። ምዕ. 2፦ መልአኩ ዑርኤል ዕዝራን መልስ ለመስጠት ይላካል። የእግዜርን ፍርድ ለማወቅ አይችልም ይለዋል። ከዚሁ ዓለም መጨረሻ ቀጥሎ በእግዜር መንግሥት ጽድቅ ዋጋውን የሚገኘው ይሆናል። እዝራ ይህ ሁሉ መቼ ይሆንን ቢጠይቀው ዑርኤል የሞቱት ጻድቃን ደግሞ ይህን ለማወቅ ፈልገው ቁጥራቸው ሳይሞላ ግን አይሆንም ብሎ መለሰለት። ለሙታን ትንሳኤ መጠበቁ ለእርግዝና መውለድን እንደ መጠበቅ ይመስላል ብሎ ጨመረለት። ምዕ. 3፦ ዑርኤል የዓለሙን መጨረሻ ሁናቴና ትልልቆቹን ምልክቶች ለእዝራ ያስረዳዋል። ከዚህ በላይ ለመማር 7 ቀን መጾም አለበት። ከ7 ቀን በኋላ ዑርኤልን እንደገና ጠይቆት የእግዜር መንግሥት ቶሎ እንዲመጣ ሰዎች ሁሉ አንድላይ ለምን አልተፈጠሩም ይላል። መሬቲቱ የሰው ልጆች ሁሉ አንዴ መውለድ ከቶ አትችልም ብሎ ዑርኤል ይመልስለታል። እግዜር የሰው ልጅ ሆኖ ወደ ፍጥረቱ እንዴት እንደሚገባ መልአኩን ይጠይቀዋል። ምዕ. 4፦ በዑርኤል አማካኝነት እግዜር እንደ ሰው ልጅ ዓለሙን ለመጎብኝት በፍጥረት መጀመርያ እንዳቀደው ይገልጽለታል። እዝራ የዚህን አለም መጨረሻ ከእግዜር መንግሥት መጀመርያ ምን ይለየዋል ቢጠይቅ፣ ያዕቆብ ከኤሳው ቀጥሎ እንደ ወጣ ይከተላል የሚል መልስ ሰጠ። ስለዚያው ዘመን ሌላ ምልክት ሲጠይቀው፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በታላቅ ድምጽ እግዚአብሔር በዓለም የኖሩትን የተነሡትን ሙታን ለመፍረድ በምጽአት መምጣቱን አዋጃ። ከዚህም የተሻለ ኑሮና ከፍተኛ ሥልጣኔ በእግዜር መንግስት ይከተላል። ዕዝራም እንደገና 7 ቀን ይጾማል። ምዕ. 5፦ ዑርኤል ተመልሶ ጠባብ መግቢያዎች ያሉት ሀገር የሚለውን ምሳሌ ይነግረዋል። አዳም በገነት በደል ባደረገ ጊዜ፣ ወደ እግዜር መንግሥት የሚሔደው መንገድ ጠባብ ሆነ ይለዋል። እግዜርን የሚንቁት በገሐነም መጥፋታቸውን ይገልጻል፣ በጎ ሥራ የሚሠሩ ግን መንግሥት ይወርሳሉ። ኅሩያን ስለሚያውቁት ጊዜያዊ መሢሓዊ መንግሥት የሚለውንም ትምህርት ይገልጻል። መሢሓዊው ንጉሥ ከሞቱ በኋላ ሰው ሁሉ ይሞታል፤ ስው ሁሉ ከሞተ በኋላ ምድር ለ7 ቀን ዝም ትላለች። ከ7ቱም ቀን በኋላ፣ የሙታን ትንሳኤ፣ ዕለተ ደይን፣ ለክፋት መሪዎችም ቅጣት፣ ለጻድቃንም መንግሥተ ሠማያት፣ ሁሉም በየተራው ይዘረዝራሉ። ምዕ. 6፦ ዕዝራ ነፍስ ከሰውነት ከተለየ በኋላ ምን ይሆናል ብሎ ይጠይቀዋል። ዑርኤልም መልሶ እስከ ትንሳዔ ድረስ ሲጠብቁ፣ የሙታን ነፍሳት ለክፉዎች ስቃይ ለጻድቃንም ሞገስ እንደሚቀበሉ የ7ቱን ሥርዓት ምስጢር ይገልጻል። በዕለተ ደይን እያንዳንዱ ግለሰብ የግል ፍርዱን ይቀበላል። ሆኖም በሕይወታቸው ገና ሳሉ ንሥሐ ከገቡ ሀጢአትን ማሸነፍ እንደሚቻላቸው ያስተምራል። ምዕ. 7፦ ዕዝራ እግዚአብሔር ምሕረት እንዲያሳይ በለመነበት ጊዜ የእግዜር መልስ ሰው ሁሉ እንዲድን አይቻልም በማለት አስጠነቀቀው። ዘርን የሚዘራው ገበሬው ያለውን ምሳሌ ይነግረዋል። በእድሜያቸው እግዜርን ከቶ ስላልፈለጉት ስለ ሀጥአን ጥፋት እንዳይጨንቅበት እዝራን ይለዋል። ዕዝራ የእግዜር መንግሥት በመጨረሻ ዘመን መቅረቡን ስለሚያሳዩት ምልክቶች እንደገና ይጠይቃል። ምዕ. 8፦ እግዜር ዕዝራን እንደሚለው፣ ያስተማራቸውን የመጨረሻ ዘመን ምልክቶችን ሰው መፈልግ አለበት። የዝንጉ ሰዎችና የታማኝ ሰዎች እድሎች ምስጢር ደግሞ ይናገራል። ከዚያ ዕዝራ ለ7 ቀን በምድረ በዳ ፍራፍሬን ብቻ እየበላ እንዲቆይ አዘዘው። ከ7ቱ ቀንም በኋላ፣ በልጇ ላይ እያለቀሰች አንዲትን ሴት ያገኛል። ምዕ. 9፦ ዕዝራ ካለቀሰችው ሴት ጋር ለመወያየት ሲወድድ፣ ድንገት አገር ሆነችና መልአኩ ተመልሶ እርሷ በዚሁ አለም የእግዚአብሔር መንግሥት ሥር ምሳሌ ኢየሩሳሌም መሆኗን ይገልጽለታል። ምዕ. 10፣ 11፦ ነቢዩ ዳንኤል ቀድሞ እንዳየ ሁሉ፣ ዕዝራ የባቢሎን ተከታይ መንግሥታት መጨረሻ ሁናቴ የሚገልጽ ራዕይ ያያል። ነገር ግን ያልታወቁ አዛጋጆች አስተሳሰባቸውን ወደ ኢትዮጵያዊው ትርጉም አስገብተዋል። እነዚህ ምዕራፎች በሌሎቹ ልሳናት (ሮማይስጥ፣ ፅርዕ፤ ወዘተ.) ለጠፋው ዕብራይስጥ ቅጂ የተሻለውን ትርጉም እንዳላቸው ይሆናል። በቅንፍ ውስጥ ስለ አፊፋኖስ አንጥያኮስ የተጨመረው ቋንቋ መቸም አልተገኘበትም። አፊፋኖስ በ2ኛ መቶ ዘመን ዓክልበ. ስለ ኖረ እንጂ፤ ራዕዩ ግን በተለይ ስለዚሁ አለም መጨረሻ ጥፋት ዘመን ነው። ክርስቶስ ከአፊፋኖስ በኋላ ኖሮ የዳንኤል ራእይ ገና ወደፊት ነው በግልጽ ቢያስተምርም፣ አይሁዶች ግን ዳንኤል ስላለፈው አፊፋኖስ ትንቢት ተናገረ ብለው አስተማሩ። ይህ የአይሁዶች ትምህርት በቅንፉ ውስጥ መታየቱ ስንኳ ጥንታዊነቱን ይመስክራል። ቅንፉን ያስገባው የከስሙናይን ሥርወ መንግሥት ደጋፊ እንደ ነበር ይመስላል (11፡32 ይዩ)። የሚከተለው ከሮማይስጥ / ፅርዕ ትርጉሞች ይወሰዳል፦ በሕልሙ ሳለ፤ ዕዝራ ባለ ሦስት ራስ ንሥር ወይም አሞራ ያያል። 12 ታላላቅ ክንፎችም አሉበት። እነዚህም 12 ታላላቅ ክንፎች እያንዳንዱ በየተራው ይገዛሉ። 2ኛው ታላቅ ክንፍ ከሌሎቹ ሁሉ የረዘመው ዘመነ መንግሥት ይቀበላል። ከርሱም ዘመን በኋላ ድምጽ ከንሥር ሰውነት ይናግራል። «ከዚህ በኋላ የመጡት ክንፎች እንደዛኛው ክንፍ ብዙ ዘመኖች እንዳይቀበሉ፣ ያኛው ክንፍ ከተቀበሉት ዘመኖች ግማሽ ይልቅ አይበልጡ» ይጮሃል። ከዚያ በኋላ የተረፉት ታላላቅ ክንፎች እስከ 12ኛው ታላቅ ክንፍ ድረስ ዘመኖቻቸውን ይጨርሳሉ። በመካከላቸው ደግሞ፣ መንግሥት ሊወድቅ እንደሚል ቢመስልም፣ ሆኖም መንግሥት የዛኔ አይወድቅም። ከ12ቱ ታላላቅ ክንፎች ቀጥሎ፣ 8 ትንንሽ ክንፎች ይነሣሉ። እነዚህ ሁሉ እስከ ንጉሥ ማዕረግ ድረስ አይደርሱም፤ አንዳንድ ምክትሎች ብቻ ናቸው። መጀመርያ ሁለት ከድንገት በዘመናቸው መካከል ይጠፋሉ። የሚከተሉ ሁለት ዘውድን በመጫን ፋንታ፡ ወደ ቀኝ ባለው ራስ ውስጥ መቆየት ይመርጣሉ። (እኚህ ሦስት ራሶች የንሥሩ መንግሥት ምንጮች ይባላሉ።) ከዚህ መንግሥታዊ ቀውስ የተነሣ፣ 4 ትንንሽ ክንፎች ይተርፋሉ። ከነዚህ አራት 1ኛው ትንሽ ክንፍ ለአጭር ዘመን ብቻ ይገዛል፤ 2ኛው ከዚያ ያነሰ እጅግ አጭር ዘመን ይቆያል። የተረፉት 2 ክንፎች ሊገዙ ሲሉ፤ ድንገት ከንሥሩ 3 ራሶች መካከለኛው ራስ ይነሣል፤ እርሱም ከሁሉ ጨካኝ የሆነ የአለም ንጉሥ ይሆናል። ከታላቁ መከራ አመታት በኋላ ግን በአልጋ ላይ ይሞታልና ወደ ቀኝ ራስ የሄዱት 2ቱ ትንንሽ ክንፎች የዛኔ ለጥቂት ዘመን ይገዛሉ። በነርሱ ዘመን ግን ብሔራዊ ጦርነት አለና አለም በእሳት ይጠፋል። በተጨማሪ አንበሳ (መሢኅ) ንሥሩን በፍጹም ይገስጻል። ምዕ. 12፦ ሰባት ቀን ካለፉ በኋላ ዕዝራ በሌላ ራዕይ አንድ ሰው ከባሕር ሲወጣ ያያል። ሠራዊቶች ሊዋጉ ሲሉ፣ ሰውዬው ተራራን ፈጥሮ ይቀመጥበታልና እሳት ከአፉ እስትንፋሽ ወጥቶ ያጠፋቸዋል። ከዚያ በኋላ ሌላ ሕዝብ ወደርሱ በሰላም ይመጣል። ከዚያም መልዓኩ የራዕዩን ፍች ይሰጠዋል። ይህ ምዕራፍ በአማርኛ ዲዩትሮካኖን እንደገና ከለሎቹ ትርጉሞች (ከጽርዕ ወዘተ.) ይለያል። በሌሎቹ ትርጉሞች ዘንድ፣ ይህ ራዕይ ስለመሢሁ መጨረሻ ምጽአት መሆኑ ግልጽ ነው። የተራራውም ትርጉም ደብረ ጽዮን ወይም የእግዚአብሔር መንግሥት ይባላል። አገሮች ሁሉ በጦርነት ተይዘው ዝም ብሎ በተራራ ላይ ይታያልና ካሸነፋቸው በኋላ ምድርን ለዘላለም ይገዛል። የአማርኛ ትርጉም ግን እንደገና በሌላ አስተያየት ተዛባ፤ በዚያ ውስጥ ተራራ መስቀል ሆኗል፤ ራዕዩም ስለዚሁ አለም መጨረሻ ቀን ሳይሆን፣ ስለ ክርስቶስ ስቅለት የሚተነብይ ሆኗል። አዋልድ መጻሕፍት
39751
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AD%E1%8B%8B%E1%88%9C%20%E1%8A%95%E1%8A%AD%E1%88%A9%E1%88%9B%E1%88%85
ክዋሜ ንክሩማህ
ክዋሜ ንክሩማህ የተወለዱት በ1909 እ.ኤ.አ. ደቡባዊ ምዕራብ ጋና (ቀደም ሲል ጎልድ ኮስት) ንክሮፉል በምትባል ከተማ ነው። ንክሩማህ በካቶሊክ ሚሽነሪ ትምህርት ቤት ይማሩበት በነበረ ወቅት ብሩህ አዕምሮ እንደነበራቸው የተመሰከረላቸው ሲሆን ገና በአሥራዎቹ እድሜ ውስጥ እያሉ ነው በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪ የሆኑት። ይሁንና ያለሥልጠና የጀመሩትን ትምህርት በ1926 እ.ኤ.አ. የአክራውን አቺሞታ ኮሌጅ ተቃለቅለው የመምህርነት ምሥክር ወረቀት በማግኘት በተለያዩ የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች አስተምረዋል። በ1935 እ.ኤ.አ. ወደ አሜሪካ በማቅናትም የፔንሴልቬኒያውን ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ተቀላቅለው በኢኮኖሚክስና ሶሲዮሎጂ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በ1939 የተቀበሉ ሲሆን በ1942ም በሥነ-መለኮት ሌላ ድግሪ ከዚሁ ዪኒቨርሰቲ አግኝተዋል። በ1942 እና በ1943ም የማስተርስ ድግሪያቸውን ከፔንሴልቬኒያ ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ትምህርትና በፍልስፍና ሠርተዋል። በአሜሪካ ቆይታቸውም በግራ ዘመም አሰተሳሰቦች በመማረከቸው የተነሳ በወቅቱ በሥርነቀል ለውጥ ፈላጊነታቸው ከሚታወቁ ምሁራን ጋር ቅርብ ግንኙነት መሥርተው ነበር። አፍሪካውያንን ያሰባሰበ የተማሪዎች እንቅስቃሴ መሥራችና ግንባር ቀደም ተናጋሪ እንዲሁም የአፍሪካ አገራት ነፃ እንዲወጡና የአውሮፓ ቅኝ ግዛት እንዲያበቃ ቁርጠኛ አቋም ነበራቸው። ከዚሁ ጎን ለጎንም የተባበረች አፍሪካ አስፈላጊነትን በማመን አፍሪካውያንና የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው ሕዝቦች በአንድነት እንዲቆሙ የሚሰብከው ፓንአፍሪካኒዝም አቀንቃኝ ነበሩ። በ1945 ወደ ለንደን ሕግና ኢኮኖሚክስ ለማጥናት ባመሩበት ወቅትም በማንችስተር እንግሊዝ የተካሄደውን 5ኛው የፓን አፍሪካን ጉባዔ እንዲካሄድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የአፍሪካን ከቅኝ ግዛት የመውጣት እንቅስቃሴ ለማስተባበርና ቅኝ አገዛዝን ለመቃውም የተደራጀው ጉባዔ ንክሩማህ ታዋቂ የጥቁር መብት ታጋዮችና የፀረ-ቅኝ ግዛት ንቅናቄ መሪዎች ጋር እንዲገናኙ ዕድል የሰጣቸው ሲሆን በ1946ም ጥናታቸውን ትተው በ5ኛው ጉባኤ የተቋቋመው የምዕራብ አፍሪካ ብሔራዊ ጽ/ቤት ዋና ጸኃፊና የምዕራብ አፍሪካ ተማሪዎች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል። ከዚያም በ1947 ወደ አገራቸው በመመለስ የጎልድኮስት ኮንቬንሽን ፓርቲ ዋና ጸኃፊ በመሆን በመላው አገሪቱ እየዞሩ ሕዝቡን ለፀረ-ቅኝ አገዛዝ ትግሉ የሚያነሳሱ ቅስቃሳዎችን አድርገዋል። በ1948 የበለጠ ሥር-ነቀል ባህርይ ያለው ኮንቬንሽን ፒውፕልስ ፓርቲ የሚባል የፖለቲካ ድርጅት የበማቋቋም ተከታታይ አድማዎችንና ተቃውሞችን በማደራጀት ቅኝ ገዥው ኃይል የማሻሻያ እርምጃዎችን እንዲወስድ ማስገደድ ችለዋል። ንክሩማህ በእስር ቤት ሆነው የተሳተፉበትን የ1951 ምርጫም ከእስር ቤት ሆነው ማሸነፍ ሲችሉ ፓርቲያቸውም በርካታ ወንበሮችን ማግኘት ችሎ ነበር። በቅኝ አገዛዝ ሥር በተመሰረቱ አስተዳደሮች በምርጫ በማሸነፍ ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ አገራቸውን በ1957 ጋና በሚል አዲስ ስያሜ ነፃ እንደትወጣ አደረጉ። ንክሩማህ ከነፃነት በኋላም የተዋሃደና ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት ለመመሥረት አገሪቷ ያላትን ሃብት ሁሉ አስተባብሮ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብ ወደ መሞከር ነበር የገቡት። የፓንአፍሪካኒዝም ዋነኛ አቀንቃኝ በመሆናቸውም ሌሎች የአፍሪካ አገራት ከቅኝ ግዛት ነፃ እንዲወጡ የሚታገሉ የነፃነት ንቅናቄዎችን ለጋስ ድጋፍ ከመቸር ወደ ኋላ አላሉም ነበር። በ1960ዎቹ በርካታ የአፍሪካ አገራት ነፃ መውጣትን ተከትሎም አፍሪካውያን የተባበሩት የአፍሪካ መንግሰታት የሚባል አንድ መንግሥት እንዲመሠረቱ ያላሰለሰ ጥረት አድርገዋል። ይህ ፍላጎታቸው መሳካት ባይችልም የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ አፍሪካ ኅብረት) እንዲመሠረት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። ንክሩማህ በመሪነት በቆዩበት ጊዜ ውስጥ ስኬታማ ሥራዎችን የሠሩ ቢሆንም ጠንካራና አምባገነናዊነት የተቀላቀለበት የአመራር ዘይቤያቸው የኋላኋላ በ1966 ቻይናን በመጎብኘት ላይ በነበሩበት ወቅት በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን እንዲወገዱ ምክንያት ሆኗል። ቀሪ ጊዜያቸውን በሳሞራ ሚሸሏ ጊኒ ያሳለፉ ሲሆን በ1972 ሕክምና ለማግኘት በሄዱባት ሮማኒያ ውሰጥ አርፈዋል። በ2004 ዓም የአፍሪካ ኅብረት አዲሱ ሕንፃ በተመረቀበት ሥነ-ሥርዓት አፍሪካ ለአንድነቷና ለነፃነቷ ከታገሉላት ግንባር ቀደም መሪዎች መካከል አንዱ ለሆኑትን የጋናውን ክዋሜ ንክሩማህ ሃውልት በማሠራት አክብራለች። የአፍሪካ መሪዎች
37930
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%88%98%E1%89%80%20%E1%8A%A8%E1%89%A0%E1%8B%B0
ደመቀ ከበደ
ጋዜጠኛና ደራሲ ደመቀ ከበደ ጎጃም-ሞጣ በ1976ዓ.ም ተወለደ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በሞጣ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት፤የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በሞጣ ከፍተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። ለኪነ-ጥበብ ያለውን ልዩ ፍቅር ለማጎልበት በት/ቤት ክበባትና በአራት ዓይና ጎሹ የከያንያን ማህበር ከአባልነት እስከ መሪነት ተሳትፏል።ቤተሰቦቹ እንደአብዛኞቹ ቤተሰቦች ጎበዝ ተማሪነቱን አስተውለው ህክምና ወይም ምህንድስና እንዲያጠና ቢገፋፉትም የቋንቋ አስተማሪዎቹም ሆኑ የሃይስኩል ጓደኞቹ ባሳደሩበት ተፅእኖና በንባብ ፍቅር ባደረበት ስሜት ጋዜጠኝነትን አጥብቆ ወደደ። በተለይ ነጋሽ መሀመድን፣ መዐዛ ብሩን፣ በላይ በቀለንና ታደሰ ሙሉነህን እጅግ መውደዱ ለጋዜጠኝነት ልዩ ፍቅር እንዲያድርበት አድርጓል፤ ለበዓሉ ግርማ ደግሞ ፍቅሩ የትየለሌ ነው፡ እናም ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የሚወደውን ሙያ ለማጥናት ዩኒቨርሲቲ ገባ። በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በጆርናሊዝምና ኮሙኒኬሽን በማዕረግ ተመርቋል። በዩኒቨርሲቲ ቆይታውም የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት (ጄኔራል አሴምብሊ) ሰብሳቢ፣የባህል ማዕከል የስነ-ዕሁፍ ዘርፍ ተጠሪ፣ የጆርናሊዝምና ኮሙኒኬሽን ክለብ መስራች ስራ አስፈፃሚ፣ የዩኒቨርሲቲው ጋዜጣና መፅሄት አዘጋጅ ሆኖ ከመስራቱም በላይ “የራስ ጥላ “ የተሰኘ መፅሀፍ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ እያለ አሳትሟል፡፡ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ባሳየው ከፍተኛ አፈፃፀም የ1999 ዓ.ም ከዓመቱ ምርጥ ተማሪዎች አንዱ በመሆን ከፕሬዝዳንቱ እጅ ሽልማት ተቀብሏል፡፡ ከዩኒቨርሲቲ ከወጣ በኋላም በሪፖርተር ጋዜጣ የባህልና ኪነ- ጥበብ አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል፡፡ በመቀጠልም በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት /አዲስ አበባ/ ከሪፖርተርነት እስከ ከፍተኛ አዘጋጅነት ያገለገለ ሲሆን በ2002 ዓም ከሬድዮ ፋና የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኞች አንዱ በመሆን ከዋና ስራ አስፈፃሚው የገንዘብና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተቀብሏል፡፡ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት የስልጠና ፕሮግራም ማሻሻያ ክፍል ተ/ኃላፊ ሆኖ ሰርቷል፣ አሁን በድርጅቱ የዜና ዋና አዘጋጅ/አስተባባሪ/ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ ደራሲው በ2003 ዓ.ም በኢትዮጵያና በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በምልክት ቋንቋ፣ በብሬል፣ በኦዲዮ ሲዲና በቴክስት በማሳተም በኢትዮጵያ ብሄራዊ ትያትር ሚኒስትሮች፣ ምሁራን፣ታላላቅ ሰዎችና አርቲስቶች በተገኙበት አስመርቋል። የመፅሃፉን ማስታዎሻነት ለታሪክ ተመራማሪውና ለኢትዮጵያ ጥናት ተቋም መስራች ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት፣ለፊስቱላ ሆስፒታል መስራች ዶ/ር ካትሪን ሀምሊን፣ ለኦርኬስትራ ኢትዮጵያ መሰራችና ማሲንቆ ተጫዋች ሚስተር ቻርለስ ሳተን፣ ለኢትዮፒክስ ተከታታይ ሲዲ አሳታሚ ፍራንሲስ ፋልሴቶና በስማቸው ጎዳና ለተጠራላቸው ሚስተር ካላራቦስ ባምቢስ ሰጥቷል፣ በምረቃው እለት በክብር እንግድነት ከተገኙት ምሁራን አንዱ የነበሩት ፕሮፌሰር አንድሪያስ እሼቴ ደራሲው ያዘጋጀውን የማስታዎሻ ስጦታ ለፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት በክብር ሰጥተውለታል። ደራሲና ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ ለታዋቂ ዘፋኞች ከሰጣቸው የግጥም ስራዎች በተጨማሪ በርካታ ለህትመት የተዘጋጁ ስራዎችን አዘጋጀቶ የህትመት ብርሃን እንዲያገኙ እየተጠባበቀ ነው። የከዋክብት ጉማጅ-አጫጭር ታሪኮች ሌዋታ- ረጅም ልቦለድ የመጀመሪያዎቹ መጀመሪያ- የታላላቅ ኢትዮጵያውያን ታሪክ ዘባሲል- ተረት፣ሳይንስ፣ሃይማኖትና ልቦለድ በአንድ ስንስል የተጣመሩበት ረጅም መፅሃፍ እና አሁን ደግሞ የህፃናትን ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት አደይ አበባ የተሰኘ ተከታታይ የልጆች አዝናኝና አስተማሪ መፅሃፍ አዘጋጅቶ በህትመትና በስርጭት አብረውት የሚሰሩ አካላትን እየጋበዘ ይገኛል። በ 2020 በኢትዮጵያ ባህርዳር ከተማ በተካሄደ የጣና ሽልማት መድረክ ላይ በኢትዮጵያ ፈጣን ወቅታዊና ሚዛናዊ መረጃ ማድረስ በሚለው ዘርፍ አሸናፊ ሆኖ ተሸልሟል።
3586
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%83%E1%8A%91%20%E1%8A%90%E1%8C%8B
ብርሃኑ ነጋ
ውልደትና እድገት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ 1958 እ.ኤ.አ. ከታዋቂው ነጋዴ የአቶ ነጋ ቦንገር እና ከወይዘሮ አበበች ወልደጊዮርጊስ በደብረ ዘይት ከተማ ተወለዱ። እድሜያቸውም 17 ዓመት እንደሞላ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የከፍተኛ ትምህርት መከታተል ጀመሩ።በወቅቱ ገዢውን የደርግ መንግስትን በመቃወም በተካሄደው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ተሳትፈዋል። በ1977 መንግስት በፖለቲካ ተቃዋሚዎች ላይ እርምጃ ሲወስድ ብርሃኑ ከሌሎች አክራሪ ተማሪዎች ጋር ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ አሲምባ ተራራ ተሰደደ። በኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ውስጥ ከተፈጠረው መከፋፈል በኋላ፣ በኢሕአፓ ውስጥ የተፈጸሙ ግድያዎችን በግልጽ በመተቸቱ ታስሯል። ከጥቂት ወራት በኋላ በአጋቾቹ ተፈትቶ ወደ ሱዳን ተሻግሮ ለሁለት አመታት የኖረበት ሲሆን በአሜሪካ የፖለቲካ ጥገኝነት እስኪሰጠው ድረስ። በኒውዮርክ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በኒው ፓልትዝ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በኢኮኖሚክስ ያጠናቀቁ ሲሆን በኒውዮርክ ከተማ ከሚገኘው ከኒው ሶሻል ጥናትና ምርምር ትምህርት ቤት በኢኮኖሚክስ ፒኤችዲ አግኝተዋል። በዚያን ጊዜም በክፍለ አህጉሩ ያለውን ፖለቲካዊ፣ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችን ተንትኖ የሚተነትን "የአፍሪካ ቀንድ" ዓመታዊ ኮንፈረንስ አዘጋጆች አንዱ ሆነዋል። ከአምስት ዓመታት በላይ በፖለቲካ መሪዎች፣ የፖሊሲ ተንታኞች እና በአፍሪካ ክፍል ለሚደረጉ ለውጦች ፍላጎት ባላቸው ተመራማሪዎች መካከል የእውቀት ውይይት መድረክ ሆኖ አገልግለዋል። የዶክትሬት ትምህርቱን በማጠናቀቅ በቡክኔል ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ፋኩልቲ ተቀላቀለ፣ ከዚያም ለሦስት ዓመታት በኢኮኖሚክስ መምህር ሆኑ። በኋላ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ፣ማህበራዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር እምቢልታ የተባለ በየሁለት ወሩ የሚታተም መፅሄት መስርቶ ይንቀሳቀሱ ነበር በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር መስራች ሊቀመንበር ነበር። ወደ ኢትዮጵያ ተመለስ ብርሃኑ ከባለቤቱ እና ከሁለቱ ልጆቹ ኖህ እና ኢያሱ ጋር በ1994 ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ።ብርሃኑ ስራ ፈጣሪ ሆኖ የኢትዮጵያ አግሮ-በቆሎ የማዳበሪያ አምራች ኩባንያ እና አዲስ መንደር ቤተሰብ ቤት ገንቢዎች መሰረተ። ብርሃኑ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል በመምህርነት አገልግሏል። ከ1996 እስከ 2000 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ለመመስረት የረዱት ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ኃላፊ በመሆን አገልግለዋል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የማማከር ስራ ሰርተዋል። ሚያዚያ 8 ቀን 2001 ብርሃኑ እና ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በብሔራዊ ሎተሪ አዳራሽ የአካዳሚክ ነፃነትን አስመልክቶ ቀኑን የሚቆይ የፓናል ውይይት ያደረጉ ሲሆን በመቀጠልም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ የተማሪዎች ተቃውሞ ተካሂዷል። የታሰሩት ይህ ፓናል በማግስቱ በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የተማሪዎች ተቃውሞ አነሳስቷል በሚል ክስ ቢሆንም ሰኔ 5 ቀን በዋስ ተለቀቁ እንጂ አንዳቸውም ፍርድ ቤት አልቀረቡም። የ2005 ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በምርጫ 2005 ብርሃኑ መለስ ዜናዊን ተከራክሯል። ከምርጫው በኋላ የፖለቲካ አለመግባባት ቢፈጠርም ከ138ቱ የከተማው ምክር ቤት 137 መቀመጫዎች ውስጥ 137ቱን ያገኙት የ አባላት ነሀሴ 20 ቀን 2009 ዓ.ም ተገናኝተው ብርሃኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ መረጡ። ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ እና አሰፋ ሀብተወልድ በምክትል ከንቲባ እና በምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ተመርጠዋል። ነገር ግን በጥቅምት ወር በተካሄደው ተቃውሞ ብርሀኑ እንዲታሰር ምክንያት ሆኗል ከየቅንጅት ሊቀመንበር አቶ ኃይሉ ሻውል፣ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም፣ የቀድሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ አቃቤ ህግ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለ ማርያም እና ሌሎች የ አመራሮች እንዲሁም በርካታ የሲቪል መብት ተሟጋቾች እና ገለልተኛ ጋዜጠኞች. የዘር ማጥፋት እና የሀገር ክህደት ወንጀል ተከሷል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና የአውሮፓ ህብረት እስረኞቹ የፖለቲካ እስረኞች መሆናቸውን አውቀው በአስቸኳይ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጠይቀዋል። ብርሃኑ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እያለ የነፃነት ጎህ ሲኬድ ("የነፃነት ጎህ)" የተሰኘ መጽሃፍ ጽፎ አሳትሟል።በመፅሃፉ ላይ እንደታተመው በኡጋንዳ ካምፓላ በኤምኤም አሳታሚ ግንቦት 2006 ይሁን እንጂ እውነተኛ አሳታሚዎች ነበሩ። አዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኘው ከአላፋ አታሚዎች ጋር በመተባበር የወጣት ምሁራን ቡድን። ከ600 ገጾች በላይ ያረጀው መጽሐፉ በከፍተኛ ደረጃ ተወዳጅነት ያተረፈ ሲሆን በመጀመሪያው ቅዳሜና እሁድ ለገበያ ቀርቦ ከ10,000 በላይ ቅጂዎችን በመሸጥ ጥቁር ገበያን በችርቻሮ 5 እጥፍ ዋጋ በማሰባሰብ - መንግስት በመጽሐፉ የተገኙ ሰዎችን ማዋከብ ጀመረ። ትራፊክ ማቆም እና መኪናዎችን መፈለግ፣ ህዝቡ የመጽሐፉን ቅጂ በጥቁር ገበያ ይሸጥ ነበር የሀገር ውስጥ አታሚዎች መጽሐፉን ለማተም ስለፈሩ ተጨማሪ ቅጂዎች ከውጭ መጡ። በ2005 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምርጫ የብርሃኑ ፓርቲ ከ138 መቀመጫዎች 137 መቀመጫዎችን አሸንፏል። ከዚያም ገዥው ፓርቲ ከተማዋን ለማስረከብ ፈቃደኛ ባለመሆኑ በስተመጨረሻ ብርሃኑን ጨምሮ የፓርቲውን አመራሮች በሙሉ አሰረ። ብርሃኑ ከ21 ወራት እስር በኋላ እስከ ሐምሌ በኢትዮጵያ አቆጣጠር 1999 ድረስ በቃሊቲ እስር ቤት ታስረው ነበር። ከሐምሌ 13 ቀን 1999 ዓ.ም. ጀምሮ መንግሥት ባደረገው ይቅርታ መሠረት ከእስር ተለቀዋል። ከተፈቱ በኋላ ወደ አሜሪካ ሄደዋል። ከሁሉም የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ጋር በመሆን በ2007 ከሀገር ወጥቶ በቡክኔል ዩኒቨርሲቲ በበክኔል ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር ሆኖ ተመልሷል። ብርሃኑ አሜሪካ በነበረበት ወቅት ግንቦት ሰባት የተባለ አዲስ የፖለቲካ ቡድን መመስረቱን አስታውቆ አሮጌው በመንግስት ፈርሷል። ህዝባዊ እምቢተኝነቱን ሁሉን አቀፍ በሆነ መንገድ ለማራመድ የተቋቋመው ግንቦት ሰባት በኢትዮጵያም ሆነ በውጭ ሀገራት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ስቧል። ግንቦት ሰባት አሁን በኢትዮጵያ ለነጻነት እና ለዲሞክራሲ ከሚታገሉ ታዋቂ ተቃዋሚ ድርጅቶች አንዱ ነው። ገዢው መንግስት ሚያዚያ 24 ቀን 2009 በግንቦት 7 አባላት የተመራውን የመንግስት ግልበጣ ሙከራ ማክሸፉን እና የሴራው አካል ናቸው ያላቸውን 35 ሰዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል። በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል ጄኔራል ተፈራ ማሞ የብርሃኑ ዘመድ ጌቱ ወርቁ እና የ80 ዓመቱ አዛውንት ፅጌ ሀብተ ማርያም በስደት በነበሩበት ጊዜ የሌላ ታዋቂ የተቃዋሚ አባት አባት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ይገኙበታል። ግንቦት 7 ይህ ውንጀላ መንግስት ተቃዋሚዎቹን ህገወጥ ተግባር በመወንጀል እና የካንጋሮ ፍርድ ቤት በመቅጣት በአጠቃላይ ተቃውሞዎችን የማፈን አካል ነው ብሏል። እ.ኤ.አ. በ2009 መጨረሻ ላይ የኢትዮጵያ ፍርድ ቤት ብርሃኑ በሌሉበት እና ከሌሎች አራት ሰዎች ጋር (በሌሉበት የተፈረደባቸው) በሞት እንዲቀጣ ወስኖ 33ቱ ደግሞ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸዋል። ብርሃኑ እ.ኤ.አ. በ2015 የፀደይ ወቅት በቡክኔል ዩኒቨርሲቲ ሙሉ ፕሮፌሰር ሆነ። እ.ኤ.አ. በጁላይ 2015 ብርሃኑ በቀይ ባህር የረዥም ጊዜ መሪ ከነበሩት የኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት እርዳታ ሲያገኙ ከነበሩት "የነጻነት ታጋዮች" ጋር ለመቀላቀል ወደ ኤርትራ ሄደ። በጥር 2016 ደጋፊዎቹን "ለማዘመን" እና ለድርጅቱ ገንዘብ ለማሰባሰብ ወደ አሜሪካ ተመለሷል። ሃገራዊ "ለውጥ" ሃገራዊ " ለውጡን" ተከትሎ በብርሃኑ ላይ የተመሠረተው ክስ ተቋርጧል ይህም ሰፊ የአንድ ወገን አካል ነው። ይቅርታ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ የሰላማዊ የፖለቲካ ተቃዋሚነት ሚናውን ለመቀጠል ችሏል። በግንቦት 2010 የብርሃኑ ግንቦት 7 ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ እና ሰማያዊ ፓርቲን ጨምሮ ከሌሎች 6 ወግ አጥባቂ-ብሔርተኛ() ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በመዋሃድ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ መሰረቱ፤ ብርሃኑ መሪ ሆኖ ተመርጧል። የትምህርት ሚኒስቴር ከ2021 የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ በኋላ በጠ/ሚ አብይ አህመድ የሚመራው የብልጽግና ፓርቲ በከፍተኛ ድምፅ አሸንፏል። በመሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዲስ መንግስት አቋቋሙ። የብርሃኑ ነጋ ፓርቲ ኢዜማ 4 መቀመጫዎችን አሸንፏል። ጠ/ሚ አብይ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት ቃል በገቡት መሠረት በምርጫው የተሳተፉትን የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ለካቢኔነት እንዲቀላቀሉ ጋብዘዋል። ጥቅምት 6 ቀን 2021 ብርሃኑ ነጋ በጠ/ሚ አብይ አህመድ የትምህርት ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። በእለቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሹመቱን ከሌሎች ሚኒስትሮች ጋር አጽድቋል። የአሁኑ የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስትር ከነሐሴ 31 2023 ጀምሮ ትምህርት ሚኒስትር ሚኒስቴርነት በድራቢነት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ተደርገው ተሹመዋል፡፡ ይህም የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ በመሆን በአዋጅ የተቋቋውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለማሳደግ ያለመ ነው ተብሏል። የግል ሕይወት ብርሃኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊት አሜሪካዊ የአይን ህክምና ባለሙያ፣ በ1989 ዶ/ር ናርዶስ ሚናሴን አግብቶ ሁለት ልጆችን አፍርተዋል - ኖህ፣ ከካርኔጊ ሜሎን ዩኒቨርሲቲ የምህንድስና ምሩቅ እና ኢያሱ፣ የፔንስልቬንያ ዩኒቨርሲቲ እና የሃርቫርድ ቢዝነስ ት/ቤት በፋይናንሺያል የተመረቀዋል። ብርሃኑ የአርሰናል ክለብ፣የክሊቭላንድ ፈረሰኞቹ እና የፊላደልፊያ ንስሮች ደጋፊ ነው። የኢትዮጵያ ሰዎች
46193
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A4%E1%88%9D%E1%8A%94%E1%88%9D
ኤምኔም
ማርሻል ብሩስ ማዘርስ (የተወለደው ኦክቶበር 17 እ.ኤ.አ 1972) ወይም በመድረክ ስሙ ኤምኔም ወይም ስሊም ሼዲ ታዋቂ የአሜሪካ ራፐር ፣ ሙዚቃ ደራሲ ፣ ሙዚቃ አቀናባሪ እና ተዋናይ ነው። ብቻውን ከሚሠራው ሥራ በተጨማሪ ፣ ዲ12 የተባለ የሙዚቃ ቡድን አባል ነው። በዓለማችን በሙዚቃ ሽያጭ ምርጥ ከሆኑ አርቲስቶች ውስጥም አንዱ ነው። በርካታ መጽሔቶችም የምን ጊዜም ታላቁ አርቲስት በማለት ይገልጹታል። ሮሊንግ ስቶን የተባለው መጽሔት ካወጣው 100 የምን ጊዜም ምርጥ አርቲስቶች መካከል በ83ኛ ደረጃ ላይም ተቀምጧል። ይህም መጽሔት የሂፕ-ሆፕ ንጉሥ በማለት ሰይሞታል። ኤምኔም ፣ ከዲ12 እና ከባድ ሚትስ ኢቭል ጋር የሠራቸውን የሙዚቃ ሥራዎችን ጨምሮ በቢልቦርድ 200 ላይ ዐሥር የሙዚቃ አልበሞቹ የአንደኝነት ደረጃን ለማግኘት በቅተዋል። ኤምኔም በዓለም አቀፍ ደረጃ ሠማንያ ሚሊየን የሙዚቃ አልበሞችና መቶ ሃያ ሚሊየን ነጠላ ዜማዎችን ሸጧል። እስከ እ.ኤ.አ ጁን 2014 ባለው መረጃ መሠረት ፣ በሙዚቃ ሽያጭ ኤምኔም የኒልሰን ሳውንድስካን ኤራ ሁለተኛ ምርጥ አርቲስት ነው። 45.16 ሚሊዮን የሙዚቃ አልበሞችንም በመሸጥ ከአሜሪካ ስድስተኛው ምርጥ አርቲስት ነው። ኤምኔም ፣ ኢንፊኒት () የተባለውን የመጀመሪያውን የሙዚቃ አልበም እ.ኤ.አ በ1996 ለቀቀ። ከዚያም በኋላ እ.ኤ.አ በ1999 ዘ ስሊም ሼዲ ኤል ፒ የተሠኘውን የሙዚቃ አልበም በመልቀቅ ስመ ጥሩነትን አገኘ። ዘ ስሊም ሼዲ ኤል ፒ ለኤምኔም ታላቅ ስኬት ነበር። ይህም አልበም በምርጥ የራፕ የሙዚቃ አልበም ዘርፍ የመጀመሪያውን የግራሚ ሽልማት እንዲያገኝ አስችሎታል። ዘ ማርሻል ማዘርስ ኤል ፒ (እ.ኤ.አ 2000) እና ዘ ኤምኔም ሾው (እ.ኤ.አ 2002) የተሠኙት አልበሞቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስኬታማነትን አግኝተዋል። ሁለቱም አልበሞች በሽያጭ ረገድ የዩ ኤስ ዳይመንድ የምስክር ወረቀት ለማግኘት ችለዋል። በተጨማሪም እነዚህ አልበሞች ምርጥ የራፕ ሙዚቃ አልበሞች በተባለው ዘርፍ የግራሚ ሽልማትን አሸንፈዋል። ይህ ደግሞ የዚህን ዘርፍ የግራሚ ሽልማት ሦስት ጊዜ በተከታታይ በማሸነፍ ኤምኔምን የመጀመሪያው አርቲስት አድርጎታል። ከዚህም በመቀጠል አንኮር () (እ.ኤ.አ 2004) የተሠኘው የሙዚቃ አልበሙ እንዲሁ ስኬታማ ነበር። ኤምኔም እ.ኤ.አ በ2005 ላይ የሙዚቃ ሥራውን ካቀረበ በኋላ ለተወሰነ ጊዜ ከመድረክ ርቆ ቆይቷል። እ.ኤ.አ በ2009 ሪላፕስ የተሠኘ የሙዚቃ አልበም ለቀቀ። እ.ኤ.አ በ2010 ደግሞ ሪከቨሪ የተሠኘ አልበም በመልቀቅ ከኤምኔም ሾው በመቀጠል ለሁለተኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የዓመቱ ምርጥ የተሸጠ አልበም ሊሆን ችሏል። ኤምኔም በሪላፕስ እና በሪከቨሪ አልበሞች የግራሚ ሽልማቶችን አግኝቷል። በሥራ ዘመኑ ሁሉ ደግሞ 13 የግራሚ ሽልማቶችን አሸንፏል። ዘ ማርሻል ማዘርስ ኤል ፒ የተሠኘውን ስምንተኛ አልበሙን እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2013 ለቅቋል። በዚህም ሁለት የግራሚ ሽልማቶችን አሸንፏል። እ.ኤ.አ በዲሴምበር 15 ቀን 2017 ሪቫይቫል የተሠኘ ዘጠነኛ አልበሙን ለቅቋል። ኤምኔም ሼዲ ሬከርድስ የተሰኘ የራሱን የሙዚቃ አሳታሚ ድርጅት እና ሌሎችም የሥራ ድርጅቶችን ከፍቷል። ሼድ 45 የተባለ የራዲዮ ጣብያም አለው። እ.ኤ.አ በ2002 ፣ ኤምኔም 8 ማይል በተባለው የሂፕ ሆፕ ድራማ ፊልም ላይ ተውኗል። በምርጥ ኦሪጂናል ዘፈን ደግሞ "ሉዝ ዩርሰልፍ" () የተሰኘው የፊልሙ ዘፈን የአካዳሚ ሽልማትን አሸንፎ ኤምኔም ይህንን ሽልማት በማሸነፍ የመጀመሪያው የራፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ ሆኗል። እና በተባሉት ፊልሞች ላይ እና አንቱራጅ () በተባለው የቴሌቪዥን ተከታታይ ፕሮግራም ላይ ብቅ ብሏል። ሕይወት እና የሥራ ዘመን እ.ኤ.አ 1972-91: የልጅነት ሕይወት ማርሻል ብሩስ ማዘርስ እ.ኤ.አ በኦክቶበር 17 1972 በሴንት ጆሴፍ ሚዙሪ ተወለደ። የማርሻል ብሩስ ማዘርስ ጁንየር እና የዲቦራ ሬ "ዴቢ" ኔልሰን ብቸኛ ልጅ ነው። ኤምኔም የእንግሊዝ ፣ የጀርመን ፣ የስኮትላንድ እና የስዊስ ዘር አለበት። ዴቢ ከብሩስ ጋር ስትተዋወቅ ገና የ14 ዓመት ልጅ ነበረች። በ17 ዓመቷ 73 ሠዓታት በፈጀው የልጇ ወሊድ ምክንያት ለሞት ተቃርባ ነበር። በወላጆቹ መሀል ቅራኔ ከመፈጠሩ በፊት ፣ "ዳዲ ዋርባክስ" () በተባለ የሙዚቃ ቡድን ውስጥ ይጫወቱ ነበር። ብሩስም ቤተሰቡን ትቶ ወደ ካሊፎርኒያ አቀና። ብሩስ ቆይቶም ሁለት ልጆችን ወለደ (ማይክል እና ሣራ)። ዴቢም ናታን "ኔት" ኬን ሳማራ የተባለውን ልጅ ወለደች። በልጅነቱ ፥ ኤምኔም እና ዴቢ አንድ ቤት ውስጥ ከአንድ ወይም ከሁለት ዓመት በላይ ሳይቆዩ በሚዙሪ እና በሚሺጋን ይመላለሱ ነበረ። በብዛትም በዘመዶቻቸው ቤት ነበር የሚቆዩት። በሚዙሪ ውስጥ የተለያዩ ከተማዎች ውስጥ ኖረዋል። ኤምኔም ዐሥራ አንድ ዓመት ሲሆነው በዋረን ሚሺጋን መኖር ጀመሩ። በታዳጊነት ዕድሜው ፥ ኤምኔም ለአባቱ ብሩስ ደብዳቤዎችን ጽፎ ነበር። ዴቢ እንደምትለው ከሆነ ፥ ደብዳቤዎቹ "ለላኪው ይመለስ" ተብለው ይመለሱ ነበር። ኤምኔም ደስተኛ ልጅ ግን ደግሞ ትንሽ ብቸኛ እንደነበር በተሰቦቹ እና ጓደኞቹ ይናገራሉ። በጉልበተኛ ልጆችም ጥቃት ይደርስበት ነበር። ዲአንጀሎ ቤይሊ የተባለ አንድ ጥቃት የፈጸመበት ልጅ ፥ ኤምኔምን ክፉኛ ከመደብደቡ የተነሳ ከባድ የጭንቅላት ጉዳት እንዲደርስበት አድርጎ ነበር። በዚህም ምክንያት እናቱ ዴቢ ኔልሰን እ.ኤ.አ በ1982 በትምህርት ቤቱ ላይ ክስ መሥረተች ፤ ነገር ግን ከአንድ ዓመት በኋላ ክሱ ተሰረዘ። ኤምኔም አብዛኛውን የማደጊያ ዓመቶቹን ያሳለፈው በዝቅተኛ የመካከለኛ የኑሮ ደረጃ ባለው እና አፍሪካዊ አሜሪካውያን በሚበዙበት በዲትሮይት አካባቢ ነው። ሂፕ ሆፕን ከማግኘቱ በፊት ፥ ኤምኔም ተረት የማውራት ዝንባሌ አድሮበት የኮሚክ መጽሐፍ አርቲስት መሆን ይፈልግ ነበር። ኤምኔም ለመጀመሪያ ጊዜ ያደመጠው የራፕ ሙዚቃ አይስ-ቲ ያቀነቀነበትን ሬክለስ () ይባላል። ይህንን ዘፈን እንደ ስጦታ የሠጠው ሮናልድ "ሮኒ" ፖልኪንግሆርን የተባለው የእናቱ የዴቢ ልጅ ነው። ከዐሥር ዓመት በኋላ ሮኒ ራሱን አጠፋ ፤ ይህም ኤምኔምን በጣም ከመጉዳቱ የተነሳ ለቀናት ያህል አይናገርም ነበር። በቀብሩም ላይም አልተገኘም። የቤት ሕይወቱ ብዙዉን ጊዜ የተደላደለ አልነበረም ፤ ከእንቱም ጋር በተደጋጋሚ ይጣላ ነበር። አንዲት የማኅበራዊ ሠራተኛም ዴቢን "በጣም ተጠራጣሪ ሴት" ብላ ትገልጻታለች። ልጇ ታዋቂ ሲሆን ፥ ጥሩ እናት አይደለችም የተባለውን በመቃወም እንዲያውም ለኤምኔም ስኬት ዋነኛው ምክንያት እንደሆነች ተናግራ ነበር። እ.ኤ.አ በ1987 እናቱ ከቤት የኮበለለችውን ኪምበርሊ አን "ኪም" ስኮት በቤታቸው እንድትቆይ ፈቀደች። ከሆኑ ዓመታት በኋላም ኤምኔም ከኪም ጋር አልፎ አልፎ ግንኙነትን ጀመረ። ከትምህርት በመቅረት እና በደካማ ውጤት ምክንያት ሦስት ዓመታትን በዘጠነኛ ክፍል ካሳለፈ በኋላ በ17 ዓመቱ ከሊንከን 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወጣ። ምንም ያህል በእንግሊዝኛ ላይ ጥልቅ የሆነ ፍላጎት ቢኖረውም (የኮሚክ መጽሐፎችን በመምረጥ) ስነ-ጽሑፍን ግን አላጠናም። ሒሳብ እና የኅብረተሰብ ትምህርትንም አይወድም ነበር። እናቱንም ለመርዳት ብዙ ሥራዎችን ይሠራ ነበር ፤ በኋላ ግን ተባረርኹ ማለት ጀመረ። እናቱ ቢንጎ ለመጫወት ከቤት ስትወጣ ፥ ሙዚቃ በኃይል ይከፍትና ግጥም ይጽፍ ነበር። እ.ኤ.አ 1992-99: የቀድሞ የሥራ ዘመን ፣ ኢንፊኒት እና ዘ ስሊም ሼዲ ኤል ፒ ታዋቂነቱ እየጨመረ በመጣ ጊዜ የተለያዩ የራፕ ቡድኖችን እንዲቀላቀል ተመልምሎ ነበር። ከነዚህም የመጀመሪያው ኒው ጃክስ () ነበር። ይህም ቡድን ከተበታተነ በኋላ ፥ እ.ኤ.አ በ1995 ነጠላ ዜማ የለቀቁትን ሶል ኢንቴንት () የተባለውን ቡድን ተቀላቀለ። በዚህ ነጠላ ዜማ ላይ ጓደኛው ፕሩፍ አቀንቅኖበት ነበር። እኚህ ሁለት ራፐሮች ተነጥለው በመውጣት ዲ12ን መሠረቱ። ኤምኔም ከዚያ በኋላ ለኤፍ ቢ ቲ ፕሮዳክሽንስ በመፈረም ኢንፊኒት የተሰኘውን የመጀመሪያው የሙዚቃ አልበሙን ሠራ። በዚህ አልበም ከሸፈናቸው ሃሳቦች አንዱ የተወለደችውን ሴት ልጁን በትንሽ ገቢ ለማሳደግ እንዴት እንደታገለ ነበር። በዚህ ጊዜ ፥ የኤምኔም የግጥም ዘይቤ እንደ ናስ እና ኤዚ የተባሉ የራፕ ሙዚቃ አቀንቃኞች አይነት ዘይቤ ነበር። ሥራዎቹ እንደወደፊቱ ቀልደኛ እና ቁጡ አልነበሩም። ኢንፊኒት በዲትሮይት ዲጄዎች ይህን ያህል ትኩረትን አላገኘም ነበር። ያገኘውም ምላሽ "ለምን ሮክ ኤንድ ሮል አትዘፍንም?" የሚል ነበር። ይህም በንዴት የተሞሉ እና ስሜታዊ የሆኑ ዘፈኖችን እንዲሠራ አደረገው። በዚህ ጊዜ ፥ ኤምኔም እና ኪም ስኮት ወንጀል በሚዘወተርበት ሰፈር ውስጥ አብረው ይኖሩ ነበር። ቤታቸውም በብዛት ዝርፍያ ይደርስበት ነበር። ለሆነ ጊዜም ሴንት ክሌር ሾርስ በሚገኘው ጊልበርትስ ሎጅ በተባለው ሬስቶራንት ውስጥ በወጥ ቤት እና በሳህን ማጠብ ይሠራ ነበር። ልጁ ሄይሊ ጄድ ስኮት ማዘርስ ከተወለደች በኋላ በሣምንት ለስድሳ ሠዓታት ለስድስት ወራት ያህል ሠርቶ ነበር። ለገና በዓል ጥቂት ቀናት ሲቀሩት ከሚሠራበት ከጊልበርትስ ሎጅ ሬስቶራንት ተባረረ። ስለዚህም ጊዜ ሲናገር እንዲህ ብሏል - "ጊዜው ከገና አምስት ቀናት በፊት ነበር። ይህም የሄይሊ ልደት ቀን ነበር። ለእርሷ የሆነ ነገር ለመግዛት የነበረኝ አርባ ዶላር ብቻ ነበር"። ኢንፊኒት ከተለቀቀ በኋላ የኤምኔም የአደንዛዥ ዕጽ እና የአልኮሆል ከልክ በላይ መጠቀም ወደ አልተሳካ የራሱን የማጥፋት ሙከራ ደረጃ አደረሰው። እ.ኤ.አ በማርች 1997 ከጊልበርትስ ሎጅ ለመጨረሻ ጊዜ ተባረረ። በዚህም ጊዜ ከኪም እና ከሄይሊ ጋር በእናቱ ተንቀሳቃሽ መኖሪያ ቤት ውስጥ ይኖር ነበር። ኤምኔም ፥ ጨካኝ እና ቁጡ የሆነውን ስሊም ሼዲ የተባለውን ገጸ ባህርይ ከፈጠረ በኋላ ተጨማሪ ትኩረትን ስቦ ነበር። "ስለ ግድያ እና አስገድዶ መድፈር ግጥም የሚገጥመው አደንዛዥ እፅ አዘዋዋሪ እና ደም የጠማው ዱርዬ" የሆነው ይህ ገጸ ባህርይ ፥ ንዴቱን እንዲገልጽ አስችሎት ነበር። እ.ኤ.አ 1997 ኤምኔም ዘ ስሊም ሼዲ ኢፒ የተባለውን የሙዚቃ አልበሙን በዌብ ኢንተርቴይንመንት አማካኝነት ለቀቀ። ስለ አደንዛዥ እፅ ፣ ስለ ወሲባዊ ድርጊቶች ፣ ስለ አእምሮ መታወክ እና ስለ ሁከት የሚያወሩ ሐሳቦችን የያዘው ይህ አልበም እንደ ድህነት እና የትዳር እና የቤተሰብ ችግሮችን የመሳሰሉ ቁም ነገር የያዙ ሐሳቦችን አካትቶ ነበር። ዘ ሶርስ የተሰኘው የሂፕ ሆፕ ጋዜጣም ኤምኔምን "አንሳይንድ ሃይፕ ()" በሚለው አንቀጹ ስር እ.ኤ.አ ማርች 1998 ላይ አስፍሮት ነበር። ኤምኔም ከመኖሪያ ቤቱ ከተባረረ በኋላ በእ.ኤ.አ 1997ቱ ራፕ ኦሊምፒክስ (ዓመታዊ የሆነ አገር አቀፍ የራፕ ሙዚቃ ውድድር) ላይ ለመወዳደር ወደ ሎስ አንጀለስ አቀና። በውድድሩም ሁለተኛ ወጣ ፤ በውድድሩ ቦታው የነበሩት የኢንተርስኮፕ ሬከርድስ ሠራተቾች የስሊም ሼዲ ኢፒን ቅጂ ለድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ለሆነው ለጂሚ አዮቪን ላኩለት። አዮቪን የተላከለትን ሙዚቃ ለአፍተርማዝ ኢንተርቴይንመንት ባለቤት ለሆነው ለዶክተር ድሬ አስደመጠው። ጂሚ ሙዚቃውን ካጫወተ በኋላ ፥ ድሬ የሚያስታውሰውን ሲናገር "በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ባሳለፍኩት የሥራ ዘመኔ ለሙከራ ከቀረቡ ሲዲ ወይም ካሴት ምንም አግኝቼ አላውቅም። ጂሚ ይህን ሲያጫውትልኝ 'አሁኑኑ ፈልገው' ነበር ያልኩት"። ነጭ ራፐር በመቅጠሩ በሥራ ባልደረቦቹ ብዙ ቢተችም በውሳኔው ግን ተማምኖ ነበር። "ነጭ አይደለም ወይን ጠጅ ቀለም እንኳን ብትሆን ግድ የለኝም። መሥራት ከቻልክ አብረን እንሠራለን"። ኤምኔም ኤን.ደብል ዩ.ኤን በማድመጥ ከታዳጊነት ዘመኑ ጀምሮ ከሚያደንቀው ከዶክተር ድሬ ጋር አንድ አልበም ላይ መሥራታቸው አስፈርቶት ነበር፦ "በጣም መለማመጥ አልፈለግኹም ነበር...እኔ አንድ ተራ የዲትሮይት ነጭ ልጅ ነኝ። ታዋቂ ሰዎችን አይቼ አላውቅም እንኳን ዶክተር ድሬን ይቅርና"። ከተከታታይ የሙዚቃ ሥራዎች በኋላ ግን መፍራቱን በመተው ከድሬ ጋር መሥራታቸውን ቀጠሉ። ኤምኔም እ.ኤ.አ ፌብሪዋሪ 1997 ላይ ዘ ስሊም ሼዲ ኤልፒን ለቀቀ። ምንም እንኳን የዓመቱ ታዋቂ አልበም ቢሆንም (በዓመቱ መጨረሻ ላይ የትሪፕል ፕላትነም ምስክር ወረቀት ቢያገኝም) ሁኔታው እና የሥራ አኳዃኑ ኬጅ የተባለውን የራፕ ሙዚቃ አቀንቃኝን ዓይነት ይመስላል የሚሉ ክሶች ቀርበውበት ነበር። በ"97 ቦኒ ኤንድ ክላይድ" ላይ ኤምኔም ከጨቅላ ሴት ልጁ ጋር አብረው ሄደው የሚስቱን ሬሳ ስለሚጥልበት በሚያወራው ግጥም እና በ"ጊልቲ ኮንሸንስ" ላይ ደግሞ ሚስቱን እና ፍቅረኛዋን እንዲገድላቸው ሰውዬውን እያበረታታ የሚናገረው ግጥም ይህንን አልበም ከታዋቂነቱ በተጨማሪ በጣም አነጋጋሪ እንዲሆን አድርጎት ነበር። ጊልቲ ኮንሸንስ በኤምኔም እና በዶክተር ድሬ መካከል ለብዙ ዘመን የሚቆየው ጓደኝነታቸው እና የሙዚቃ ባልደረባነታቸው መጀመሪያ ነበር። እኚህ ሁለቱ ከዚህ በኋላ በተለያዩ ሙዚቃዎች ላይ አብረው ሠርተዋል። ዶክተር ድሬም በእያንዳንዱ የኤምኔም አፍተርማዝ አልበም ላይ ቢያንስ አንድ ጊዜ ያቀነቅን ነበር። ዘ ስሊም ሼዲ ኤል ፒ የኳድሩፕል ፕላትነም ምስክር ወረቀት በአር አይ ኤ ኤ ተሰጥቶታል። እ.ኤ.አ 2000-2002: ዘ ማርሻል ማዘርስ ኤል ፒ እና ዘ ኤምኔም ሾው ዘ ማርሻል ማዘርስ ኤል ፒ እ.ኤ.አ በሜይ 2000 ተለቀቀ። በመጀመሪያው ሣምንት 1,760,000 ቅጂዎች ተሽጠው በስኑፕ ዶግ ዶጊስታይል ተይዞ የነበረውን "በፍጥነት-የተሸጠ ሂፕ ሆፕ አልበም" እና በብሪትኒ ስፒርስ ቤቢ ዋን ሞር ታይም ተይዞ የነበረውን "በፍጥነት-የተሸጠ ነጠላ አልበም" ክብረ ወሰኖችን ሰብሯል። ከአልበሙ የመጀመሪያው ዘ ሪል ስሊም ሼዲ የተባለው ነጠላ ዘፈን ምንም እንኳን በኤምኔም ስድቦች ምክንያት አነጋጋሪ ቢሆንም በጣም ስኬታማ ሆኖ ነበር። ዘ ዌይ አይ አም በሚለው ሁለተኛው ነጠላ ዘፈን ላይ እንዴት የሙዚቃ አቀናባሪ ድርጅቱ ማይ ኔም ኢዝን የሚስተካከል ሥራ እንዲሠራ እንዴት ጫና እንዳደረጉበት ይገልጻል። በሦስተኛው ነጠላ ዜማ ስታን ደግሞ ኤምኔም አዲስ ያገኘውን ዝና ለመቆጣጠር ይሞክራል። በዚህም ዘፈን ላይ እራሱን እና ነፍሰ-ጡር እጮኛውን የሚገድል አንድ የእብድ አድናቂን ገጸ ባህርይ ይዞ ይዘፍናል። ኪው መጽሔትም "ስታን" የተባለውን ነጠላ ዜማ ሦስተኛው የምንግዜም ምርጥ የራፕ ሙዚቃ ብሎ ፈርጆታል። ይህም ዘፈን በሮሊንግ ስቶን 500 የምን ጊዜም ምርጥ ዘፈኖች ውስጥ በ296ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። እ.ኤ.አ በጁላይ 2000 ፥ ዘ ሶርስ በተሰኘው መጽሔት ላይ በመውጣት ኤምኔም የመጀመሪያው ነጭ አቀንቃኝ ነበር። ዘ ማርሻል ማዘርስ ኤል ፒ የ11×ፕላትነም ምስክር ወረቀትን ከአር አይ ኤ ኤ አግኝቷል። ዘ ኤምኔም ሾው እ.ኤ.አ በሜይ 2002 ተለቀቀ። ይህም አልበም በመጀመሪያው ሙሉ ሣምንት ከ1.3 ሚሊዮን ቅጂዎች በላይ በመሸጥ በሠንጠረዦች ላይ አንደኛ ደረጃን በማግኘት ስኬታማ ሆኖ ነበር። "ዊዝአውት ሚ" በተሰኘው አንደኛው የአልበሙ ነጠላ ዜማ ላይ ሊምፕ ቢዝኪት ፣ ዲክ እና ላይን ቼኒ ፣ ሞቢ እናም የሌሎችን የተለያዩ የሙዚቃ ባንዶችን ስም አጥፍቷል። ይህም አልበም ኤምኔም ወደ ዝናው በመምጣቱ ስላመጣው ውጤት ፣ ከሚስቱ እና ከሴት ልጁ ጋር ስለነበረው ግንኙነት ፣ በሂፕ ሆፕ ማህበረሰብ ውስጥ ስለነበረው አቋም እና ሌሎች ሐሳቦችንም አካትቷል። ምንም እንኳን አንዳንድ ዘፈኖቹ በንዴት የተሞሉ ቢሆኑም እንኳን ፥ የኦል ምዩዚኩ ስቴፈን ቶማስ ኧርልዊን ዘ ኤምኔም ሾው ከዘ ማርሻል ማዘርስ ኤል ፒ አንጻር ሲታይ ለዘብተኛ ነው ብሏል። ዘ ኤምኔም ሾው የእ.ኤ.አ 2002 ምርጥ የተሸጠ አልበም ነበር። እ.ኤ.አ 2003-2007: አንኮር እና ድንገተኛ የሙዚቃ ሥራን ማቆም እ.ኤ.አ በዲሴምበር 8 2003 ላይ የዩናይትድ ስቴትስ ሲክሬት ሰርቪስ ኤምኔም የዩናይትድ ስቴትስን ፕሬዚደንት ላይ ዝቷል የሚለውን ክስ "በማጣራት ላይ" ነበር። ለዚህም ምክንያት የነበረው በአንኮር በተሰኘው አልበሙ ላይ የሚገኘው "ዊ አዝ አሜሪካንስ" በተባለው ዘፈን ምክንያት ነበር። በ2004 እ.ኤ.አ የተለቀቀው አንኮር ስኬታማ ሆኖ ነበር። ማይክል ጃክሰንን የሚያንጓጥጥ ስንኞችን የያዘው "ጀስት ሉዝ ኢት" የተባለው የአልበሙ የመጀመሪያ ነጠላ ዜማ ለአልበሙ ሽያጭ ስኬት ከፊል ሚና ተጫውቷል። በእ.ኤ.አ ኦክቶበር 12 2004 ፥ "ጀስት ሉዝ ኢት" ከተለቀቀ ከሣምንት በኋላ ፥ ማይክል ጃክሰን በሎስ አንጀለስ ወደሚገኘው የስቲቭ ሃርቪ የራዲዮ ዝግጅት ላይ በመደወል በቪዲዮው አለመደሰቱን ገለጸ። ቪድዮው በማይክል ጃክሰን ሕጻናትን በማባለግ ክስ ፣ በፕላስቲክ ቀዶ ህክምና እና በእ.ኤ.አ 1984 ላይ ማስታወቂያ ሲሰራ በፀጉሩ ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ ላይ ቀልዷል። ብዙ የማይክል ጃክሰን ጓደኞች ፥ ስቲቪ ዎንደርን ጨምሮ ፥ የሙዚቃ ቪድዮውን ተቃውመዋል። ቪድዮው እነ ፒ-ዊ ኸርመን ፣ ኤም ሲ ሃመር እና ማዶና ላይ ሁሉ ቀልዷል። ምንም እንኳን ብላክ ኢንተርቴይንመንት ቴሌቪዥን ሙዚቃውን ማጫወት ቢያቆምም ኤም ቲቪ ግን ማሠራጨቱን እንደማያቆም ገልጾ ነበር። በእ.ኤ.አ 2007 ማይክል ጃክሰን እና ሶኒ ፥ ፌመስ ምዮዚክን ከቪያኮም ገዙ ፤ ይህም ማይክል ጃክሰንን በኤምኔም ፣ በሻኪራ ፣ በቤክ እና በሌሎች አርቲስቶች ዘፈን ላይ ባለመብት አደረገው። ዋቢ ምንጮች የአሜሪካ ዘፋኞች ሂፕ ሆፕ
45037
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B6/%E1%88%AD%20%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%89%B2%E1%8A%95%20%E1%88%89%E1%89%B0%E1%88%AD%20%E1%8A%AA%E1%8A%95%E1%8C%8D
ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ
ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒዮር (እንግሊዝኛ፦ .) (1921-1960 ዓም) ስመ ጥሩ አመሪካዊ የክርስትና ሰባኪና የብሔራዊ መብቶች እንቅስቃሴ መሪ ነበሩ። ህልም አለኝ ( ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር በ1963 እ.ኤ.አ. በዋሽንግተን ዲሲ አደባባይ ለተሰበሰቡት አድማጮቹ በሰው ልጅ የነፃነትና የእኩልነት ታሪክ ውስጥ ሲጠቀስ የሚኖረውን "ህልም አለኝ" የተሰኘ ንግግሩን አሰማ፡፡ የዚህን ንግግር ኃያልነትና ጥልቀት ለመረዳት ንግግሩ የተደረገበትን ዘመን ታሪክ መለስ ብሎ መቃኘት ያስፈልጋል፡፡ ጊዜው ሩቅ አይደለም - ማርቲን ሉተር ኪንግ በአደባባይ ለጥቁሮች ጥላቻ ባላቸው ነጮች ከተገደለ እንኳን ገና ሃምሳ ዓመት መሙላቱ ነው፡፡ ዛሬም ድረስ ቅሪቶቹ በተለያየ መንገድ የሚንፀባረቁት በነጮችና በጥቁሮች መካከል የሚደረግ አድልዎ ማርቲን ሉተር ኪንግና መሰሎቹ በኖሩበት ዘመን ህጋዊ ሽፋን ያገኘ ድርጊት ነበር፡፡ ጥቁሮች በአንድ ሀገር ውስጥ አንድ ሰው ሊኖረው የሚገባው የሰውነትና የዜግነት መብቶች ተነፍገዋቸው ነበር፡፡ ጥቁሮች ፡- ከነጮች ጋር በአንድ ት/ቤት የመማር፣ ምግብ ቤት ፣ መፀዳጃ ቤት፣ የህዝብ ትራንስፖርት የመሳሰሉትን መጠቀም አይፈቀድላቸውም ነበር በፖለቲካዊ ምርጫ በመምረጥም ሆነ በመመረጥ መሳተፍ አይችሉም ነበር፡፡ እነዚህ በአደባባይ ከሚደረጉት መዋቅራዊ መድልዎች መካከል ጥቂቶቹ ብቻ ናቸው፡፡ በነጭ ግለሰቦች የሚፈፀሙ ፀያፍ የአድልዎና የጥላቻ ተግባራት ከዝርዝር በላይ ናቸው፡፡ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየርና የትግል አጋሮቹ ይህ ሰው በተፈጥሮው ሰው ስለሆነ ብቻ ሊያገኘው የሚገባውን የተፈጥሮ መብት ጨምሮ በአገሪቱ ህገ-መንግስት (እነርሱ የሪፐብሊኩ መስራች አባቶች () ብለው በሚጠሯቸው ግለሰቦች) የተፃፉትን መርሆች የሚቃረን መዋቅራዊም ሆነ ግለሰባዊ አድልዎ ኃይል ያልተቀላቀለበት አመፅ () በሆነ የትግል መንገድ ለማስቀረት እንቅስቃሴ ጀመሩ፡፡ ምንም እንኳን ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየርና መሰሎቹ አመፅ-አልባ የትግል ስልትን ቢመርጡም እነርሱ የሚታገሉት የነጮችን የበላይነት የሚያራምደው መዋቅራዊ ስርዓትም ሆነ ግለሰቦች ይህን አመፅ-አልባ ትግል ለማስቀረት የተከተሉት መንገድ ፍፁም ተቃራኒ የሆነ ነበር፡፡ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየርን ጨምሮ በዚህ አመፅ-አልባ ትግል ውስጥ የተሳተፉት ጥቁሮች ተደብድበዋል፣ ታስረዋል ተገድለዋል፡፡ ዛሬም ድረስ መዋቅራዊ ዘረኝነት () በአሜሪካ ጣጣው ያበቃ አይመስልም፡፡ በየግዛቶቹ ከዘረኝነት ጋር የተያያዙ አመፆችና ግድያዎች የየዕለት ዜና ዘገባዎች መሆናቸው አላበቃም፡፡ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየርና አጋሮቹ ይህንን ጥቁሮቹን ከሰውነትና ከዜግነት በታች ያደረጋቸውን ስርዓት ለማስቀረት አመፁ፡፡ አንዱ የአመፁ መገለጫ የአደባባይ ሰልፍ ማድረግ ነውና በሀገሪቱ ዋና ከተማ በዋሽንግተን ዲ.ሲ አደባባይ ብዙ ሺዎች ሆነው ተሰለፉ፡፡ በዚህ የ1963 እ.ኤ.አ. የአደባባይ ሰልፍ ላይ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር "ህልም አለኝ" የተሰኘ ዝነኛ ንግግሩን አሰማ፡፡ በዚህ ንግግሩ ላይ እንዲህ አለ " … ወደ ሀገሪቱ ዋና ከተማ የመጣነው የተሰጠንን ቼክ ልንመነዝር ነው፡፡ የሪፐብሊኩ መስራቾች አንፀባራቂ የሆኑትን ህገ-መንግስት ()ና የነፃነት አዋጅ () በፃፉ ጊዜ ሁሉም አሜሪካዊ ወራሽ የሚሆንበትን የቃል-ኪዳን ሰነድ () ነው የሰጡን፡፡ … ይሁን እንጂ አሜሪካ ለጥቁር ህዝቦቿ 'በቂ ስንቅ የለውም' የሚል ማህተም የተረገጠበት 'ደረቅ ቼክ' ሰጥታቸዋለች፡፡ ነገር ግን የፍትህ ባንክ ከስሯል ብለን ማመን አንፈልግም፡፡ በዚህ ሀገር ታላቅ የመጠቀም ዕድል ካዝና () ውስጥ በቂ የሆነ ሀብት የለም ብለን አናምንም፡፡ ስለሆነም ዛሬ የነፃነትን ሀብትና የፍትህን ዋስትና የሚሰጠንን ይህንን ቼክ ልንመነዝር መጥተናል፡፡" ምንም እንኳን ይህ የደረቅ ቼክ ይመንዘርልን ጥያቄ የማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየርን ህይወት ጨምሮ የብዙ ሰዎችን ህይወት ያሳጣ ቢሆንም ከግማሽ በላይ የሚሆነው ተመንዝሯል፡፡ ዛሬ ጥቁሮች ፡- የመመረጥና የመምረጥ ከነጮች ጋር በአንድ ት/ቤት የመማር፣ ምግብ ቤት ፣ መፀዳጃ ቤት፣ የህዝብ ትራንስፖርት የመሳሰሉትን የመጠቀም መብት አላቸው ነገር ግን አሁንም ቢሆን ያልተመነዘሩ ቀሪ የቼኩ ስንቆች አሉ፡፡ በግለሰብና በመዋቅራዊ ስርዓት የሚደረጉ መድሎዎች አሁንም አላቋረጡም፡፡ መሳሪያ ያልታጠቁ ጥቁሮች በታጠቁ ፖሊሶች ይገደላሉ፡፡ ጥቁሮች ከነጮቹ የበለጠ በአነስተኛ የህግ መተላለፍ ጥፋቶች የረዥም ዓመታት አሊያም የዕድሜ ልክ እስራት ይፈረድባቸዋል፡፡ በቅርቡ እንኳን በስታርባክስ የቡና መሸጫ ሰው ለመጠበቅ የገቡ ሁለት ጥቁሮች ፖሊስ ተጠርቶ እንዲታሰሩ ተደርጓል፡፡ (ምንም እንኳን በኋላ የስታርባክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ በይፋ ይቅርታ ቢጠይቅም) ይህ አይነቱ አድልዎ ) የመሳሰሉ እንቅስቃሴዎች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆኗል፡፡ በየትኛውም የዓለም ክፍል ከሚደረጉ ኃይል ካልተቀላቀለባቸው የአመፅ ታሪኮች እንደ ፋኖ ከሚጠቀሱ ባለታሪከኞች መካከል ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየርና አጋሮቹ የሆኑበት ዋነኛው ምክንያት የትግላቸው መነሻ ሰው በቆዳ ቀለሙ በማህበራዊ ህይወቱና በፖለቲካዊ ስልጣን ልዩነት የተነሳ አድልዎ ሳይደረግበት የሰውነት መብቱ ሊከበርለት ይገባል የሚል መሰረታዊ መርሆ በመያዛቸው ነው፡፡ በኢኮኖሚ ያደገም ሆነ ያላደገ ሀገርን የሚመራ ግለሰብም ሆነ ቡድን የዜጎችን ሰብዓዊና የዜግነት መብታቸውን ለማክበር ዘር፣ ሃይማኖት፣ ባህል ልማድና የቆዳ ቀለምን ለአስተዳደራዊም ሆነ ለፖለቲካዊ ጥቅምም ቢሆን መሰረት ሊያደርግ አይገባም፡፡ የአሜሪካ ሰዎች
52403
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B6%E1%88%AA%E1%8B%AB
ሶሪያ
ሶሪያ (አረብኛ፡ ወይም ፣ )፣ በይፋ የሶሪያ አረብ ሪፐብሊክ (አረብኛ፡ ፣ በምእራብ-አስያ-አራብዒህ-አስያ-አስያ-አስያ-አስያ-ጁምህ-ሀገር፣ ሮማንኛ ሶሪያ በምዕራብ የሜድትራንያን ባህርን፣ በሰሜን ቱርክ፣ ኢራቅን በምስራቅና በደቡብ ምስራቅ፣ በደቡብ ዮርዳኖስ፣ እና እስራኤል እና ሊባኖስን በደቡብ ምዕራብ ትዋሰናለች። ቆጵሮስ በምዕራብ በሜዲትራኒያን ባህር በኩል ትገኛለች። ለም ሜዳ፣ ከፍተኛ ተራራዎች እና በረሃዎች ያሉባት ሀገር፣ ሶሪያ የተለያዩ ጎሳ እና ሀይማኖታዊ ቡድኖች የሚኖሩባት ሲሆን አብዛኞቹ የሶሪያ አረቦች፣ ኩርዶች፣ ቱርክማን፣ አሦራውያን፣ አርመኖች፣ ሰርካሲያን፣ ማንዳውያን እና ግሪኮች ይገኙበታል። የኃይማኖት ቡድኖች ሱኒዎች፣ ክርስቲያኖች፣ አላውያን፣ ድሩዝ፣ ኢስማኢሊስ፣ መንዳኢያን፣ ሺዓዎች፣ ሳላፊዎች እና ያዚዲስ ይገኙበታል። የሶሪያ ዋና ከተማ እና ትልቁ ከተማ ደማስቆ ነው። አረቦች ትልቁ ጎሳ ሲሆኑ ሱኒ ደግሞ ትልቁ የሃይማኖት ቡድን ነው። ሶሪያ 14 ጠቅላይ ግዛቶችን ያቀፈች አሃዳዊ ሪፐብሊክ ስትሆን በፖለቲካዊ መልኩ ባቲዝምን የምትደግፍ ብቸኛ ሀገር ነች። ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውጪ የአንድ አለም አቀፍ ድርጅት አባል ነው። እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 2011 ከአረብ ሊግ እና ከእስላማዊ ትብብር ድርጅት ታግዶ ከህብረት ለሜዲትራኒያን ባህር እራሱን ታግዷል። “ሶሪያ” የሚለው ስም በታሪክ ሰፊ ክልልን የሚያመለክት፣ በሰፊው ከሌቫንት ጋር ተመሳሳይ ነው፣ እና በአረብኛ አል ሻም በመባል ይታወቃል። ዘመናዊው መንግሥት የ 3 ኛው ሺህ ዓመት ዓክልበ. የኤብላን ሥልጣኔን ጨምሮ የበርካታ ጥንታዊ መንግሥታት እና ኢምፓየር ቦታዎችን ያጠቃልላል። አሌፖ እና ዋና ከተማዋ ደማስቆ በአለም ላይ ካሉት ቀጣይነት ያላቸው ሰዎች ከሚኖሩባቸው ከተሞች መካከል አንጋፋዎቹ ናቸው። በእስላማዊው ዘመን ደማስቆ የኡመያ ኸሊፋነት መቀመጫ እና የግብፅ የማምሉክ ሱልጣኔት ግዛት ዋና ከተማ ነበረች። ዘመናዊው የሶሪያ መንግስት የተመሰረተው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ከዘመናት የኦቶማን አገዛዝ በኋላ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በኋላ እንደ ፈረንሣይ ሥልጣን አዲስ የተፈጠረችው መንግሥት በኦቶማን ይመራ ከነበረው የሶሪያ ግዛት የወጣችውን ትልቁን የአረብ መንግሥት ይወክላል። በጥቅምት 24 ቀን 1945 የሶሪያ ሪፐብሊክ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መስራች አባል በሆነችበት ጊዜ ዴ ጁር ነፃነቷን እንደ ፓርላሜንታዊ ሪፐብሊክ አገኘች ፣ ይህ ድርጊት በሕጋዊ መንገድ የቀድሞውን የፈረንሳይ ማንዴት ያቆመ ፣ ምንም እንኳን የፈረንሳይ ወታደሮች እስከ ኤፕሪል 1946 ሀገሪቱን ለቀው ባይወጡም ። ከ1949 እስከ 1971 ድረስ ብዙ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት እና መፈንቅለ መንግስት ሙከራዎች ሀገሪቱን አንቀጠቀጠ።ከነጻነት በኋላ የነበረው ጊዜ ውዥንብር ነበር።በ1958 ሶሪያ ከግብፅ ጋር የተባበሩት አረብ ሪፐብሊክ የተባለች አጭር ህብረት ፈጠረች፣ይህም በ1961 የሶሪያ መፈንቅለ መንግስት ተቋረጠ። . ሪፐብሊኩ በ1961 መጨረሻ ላይ የሶሪያ አረብ ሪፐብሊክ ተብሎ ተሰይሟል እ.ኤ.አ. በታህሣሥ 1 የሕገ መንግሥት ሕዝበ ውሳኔ በኋላ፣ እና እስከ 1963 የባአትስት መፈንቅለ መንግሥት ድረስ የተረጋጋ ነበር፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ባአት ፓርቲ ሥልጣኑን አስጠብቆ ቆይቷል። ሶሪያ ከ1963 እስከ 2011 በአደጋ ጊዜ ህግ ስር ነበረች፣ ይህም ለዜጎች የሚሰጠውን አብዛኛዎቹን ህገ-መንግስታዊ ጥበቃዎች ውጤታማ በሆነ መንገድ አግዷታል። ባሽር አል አሳድ እ.ኤ.አ. ከ 2000 ጀምሮ በፕሬዚዳንትነት የቆዩ ሲሆን ከ 1971 እስከ 2000 በስልጣን ላይ የነበሩት አባቱ ሃፌዝ አል-አሳድ ነበሩ።በስልጣን ዘመናቸው ሁሉ ሶሪያ እና ገዥው ባአት ፓርቲ በተለያዩ የሰብአዊ መብት ጉዳዮች ሲወገዙ እና ሲተቹ ቆይተዋል። በዜጎች እና በፖለቲካ እስረኞች ላይ ተደጋጋሚ ግድያ እና ከፍተኛ ሳንሱርን ጨምሮ የመብት ጥሰቶች። እ.ኤ.አ. ከመጋቢት 2011 ጀምሮ ሶሪያ በባለብዙ ወገን የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ትገኛለች ፣በቀጣናው እና ከዚያ በላይ ባሉ በርካታ ሀገራት በወታደራዊም ሆነ በሌላ መልኩ ተሳትፎ አድርገዋል። በዚህም ምክንያት፣ በሶሪያ ግዛት ላይ በርካታ ራሳቸውን የፖለቲካ ነን የሚሉ የሶሪያ ተቃዋሚዎች፣ ሮጃቫ፣ ታህሪር አል ሻም እና እስላማዊ መንግስት ቡድንን ጨምሮ ብቅ አሉ። ሶሪያ ከ 2016 እስከ 2018 በአለም አቀፍ የሰላም መረጃ ጠቋሚ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች, ይህም በጦርነቱ ምክንያት በአለም ላይ ከፍተኛ ጥቃት የሚደርስባት ሀገር አድርጓታል. ግጭቱ ከ570,000 በላይ ሰዎችን ገድሏል፣ 7.6 ሚሊዮን ተፈናቃዮችን አስከትሏል (የጁላይ 2015 ግምት) እና ከ5 ሚሊዮን በላይ ስደተኞች (ጁላይ 2017 በ ተመዝግቧል) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የህዝብ ግምገማ አስቸጋሪ አድርጎታል። ሥርወ ቃል ብዙ ምንጮች እንደሚያመለክቱት የሶሪያ ስም ከክርስቶስ ልደት በፊት በ8ኛው ክፍለ ዘመን ከሉዊያውያን ቃል "ሱራ/ኢ" ሲሆን የጥንታዊው የግሪክ ስም፡ ፣ ወይም ፣ ስይሮይ፣ ሁለቱም በመጀመሪያ ከአሽሽዩሪያዩ () የመጡ ናቸው። ሜሶፖታሚያ ነገር ግን፣ ከሴሉሲድ ኢምፓየር (323-150 ዓክልበ.) ይህ ቃል ለሌቫንትም ተተግብሯል፣ እናም ከዚህ ነጥብ ግሪኮች ቃሉን በሜሶጶጣሚያ አሦራውያን እና በሌዋውያን አራማውያን መካከል ያለ ልዩነት ተጠቀሙበት። የሜይንስትሪም ዘመናዊ አካዳሚክ አስተያየቶች የግሪክ ቃል ከኮኛት ፣ አሦር፣ በመጨረሻም ከአካዲያን አሹር የተገኘ ነው የሚለውን መከራከሪያ በጥብቅ ይደግፋል። የግሪኩ ስም ፊንቄያን "አሱር"፣ "አሦራውያን" ጋር የሚዛመድ ይመስላል፣ በ8ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. ጽሑፍ ላይ ተመዝግቧል። በቃሉ የተሰየመው ቦታ በጊዜ ሂደት ተለውጧል። በጥንታዊ መልኩ፣ ሶሪያ በሜዲትራኒያን ምሥራቃዊ ጫፍ፣ በአረብ ወደ ደቡብ እና በትንሿ እስያ በሰሜን መካከል ትገኛለች፣ ኢራቅን በከፊል ለማካተት ወደ ውስጥ ተዘርግታለች፣ እና ሽማግሌው ፕሊኒ ከምዕራብ እንደሚጨምር የገለፀው በሰሜን ምስራቅ በኩል እርግጠኛ ያልሆነ ድንበር አላት ወደ ምስራቅ፣ ኮማጌኔ፣ ሶፊኔ እና አዲያቤኔ። በፕሊኒ ጊዜ ግን ይህች ትልቋ ሶርያ በሮማ ኢምፓየር ስር ወደተለያዩ አውራጃዎች ተከፋፍላለች (ነገር ግን በፖለቲካዊ መልኩ አንዳቸው ከሌላው ነጻ ናቸው)፡ ይሁዳ፣ በኋላም ፓሌስቲና የተባለችው በ135 ዓ.ም. ግዛቶች, እና ዮርዳኖስ) በደቡብ ምዕራብ ጽንፍ; ፊንቄ (በ194 ዓ.ም. የተመሰረተ) ከዘመናዊ ሊባኖስ፣ ደማስቆ እና ሆምስ ክልሎች ጋር የሚዛመድ; ኮሌ-ሶሪያ (ወይም “ሆሎው ሶሪያ”) እና ከኤሉቴሪስ ወንዝ በስተደቡብ። የጥንት ጥንታዊነት ሶሪያ የኒዮሊቲክ ባህል ማዕከላት አንዱ ነበር (ቅድመ ሸክላ ኒዮሊቲክ ኤ በመባል የሚታወቀው) ግብርና እና የከብት እርባታ በዓለም ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ከታዩበት። የሚከተለው የኒዮሊቲክ ጊዜ () በሙሬቤት ባህል አራት ማዕዘን ቅርፅ ያላቸው ቤቶች ይወከላል። በቅድመ-የሸክላ ስራ ኒዮሊቲክ ዘመን ሰዎች ከድንጋይ, ከጂፕስ እና ከተቃጠለ ሎሚ (ቫስሴል ብላንች) የተሠሩ መርከቦችን ይጠቀሙ ነበር. ከአናቶሊያ የተገኙ የ መሳሪያዎች ግኝቶች ቀደምት የንግድ ግንኙነቶች ማስረጃዎች ናቸው። የሃሙካር እና የኤማር ከተሞች በኒዮሊቲክ እና የነሐስ ዘመን መገባደጃ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። አርኪኦሎጂስቶች በሶርያ ውስጥ ያለው ሥልጣኔ በምድር ላይ ካሉት እጅግ ጥንታዊ ከሚባሉት አንዱ እንደሆነና ምናልባትም ቀደም ሲል በሜሶጶጣሚያ ብቻ እንደነበረ አረጋግጠዋል። በክልሉ ውስጥ ቀደምት የተመዘገበው የአገሬው ተወላጅ ሥልጣኔ በዛሬዋ ኢድሊብ፣ ሰሜናዊ ሶሪያ አቅራቢያ የሚገኘው የኤብላ መንግሥት ነው። ኤብላ በ3500 ዓክልበ. አካባቢ የተመሰረተች ትመስላለች፣ እና ቀስ በቀስ ሀብቷን ከሜሶጶጣሚያ ግዛቶች ሱመር፣ አሦር እና አካድ እንዲሁም በሰሜን ምዕራብ ካሉት ከሁሪያን እና ከሃቲያን ህዝቦች ጋር በመገበያየት በትንሿ እስያ። በቁፋሮ ወቅት የተገኙት የፈርዖኖች ስጦታዎች ኤብላ ከግብፅ ጋር ያላትን ግንኙነት አረጋግጠዋል። ከሶሪያ የመጀመሪያዎቹ የተጻፉ ጽሑፎች አንዱ የኤብላው ቪዚየር ኢብሪየም እና አባርሳል ሐ በሚባል አሻሚ መንግሥት መካከል የተደረገ የንግድ ስምምነት ነው። 2300 ዓክልበ.. የኤብላ ቋንቋ ከአካድያን ቀጥሎ ከታወቁት ጥንታዊ የሴማዊ ቋንቋዎች አንዱ እንደሆነ ሊቃውንት ያምናሉ። የኤብላይት ቋንቋ በቅርብ ጊዜ የተከፋፈለው የምስራቅ ሴማዊ ቋንቋ ነበር፣ ከአካድ ቋንቋ ጋር በቅርበት ይዛመዳል። ኤብላ ከማሪ ጋር ባደረገው ረዥም ጦርነት ተዳክማለች፣ እና መላው ሶርያ የሜሶጶጣሚያ አካድ ግዛት አካል ሆነች በኋላ የአካድ ሳርጎን እና የልጅ ልጁ ናራም-ሲን ወረራ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ23ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ ኤብላን በሶርያ ላይ የገዛውን የበላይነት ካቆመ በኋላ። በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ, ሁሪያኖች በሰሜናዊ ምስራቅ የሶርያ ሰሜናዊ ክፍል ሲሰፍሩ የተቀረው አካባቢ በአሞራውያን ተገዝቷል. ሶርያ በአሦር ባቢሎን ጎረቤቶቻቸው የአሙሩ (አሞራውያን) ምድር ተብላ ትጠራ ነበር። በከነዓናውያን ቋንቋዎች የተረጋገጠው የአሞራውያን የሰሜን ምዕራብ ሴማዊ ቋንቋ ነው። ማሪ በዚህ ጊዜ ውስጥ እንደገና ተነሳች እና በባቢሎን ሀሙራቢ እስኪያሸንፍ ድረስ የታደሰ ብልጽግናን አይታለች። ኡጋሪት እንዲሁ በዚህ ጊዜ ውስጥ ተነሳ፣ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1800 አካባቢ፣ ለዘመናዊቷ ላታኪያ ቅርብ። ኡጋሪቲክ የሴማዊ ቋንቋ ከከነዓናውያን ቋንቋዎች ጋር በቀላሉ የሚዛመድ ሲሆን የኡጋሪቲክ ፊደላትን ያዳበረ ሲሆን ይህም በዓለም የመጀመሪያ ደረጃ የታወቀ ፊደል ተደርጎ ይቆጠር ነበር። የኡጋሪት መንግሥት በ12ኛው ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኋለኛው የነሐስ ዘመን ውድቀት ተብሎ በሚታወቀው የኢንዶ-አውሮፓ ባህር ሕዝቦች እጅ እስከ ጠፋበት ጊዜ ድረስ ተመሳሳይ መንግሥታትና ግዛቶች ተመሳሳይ ጥፋት በባህር ሕዝቦች እጅ ሲወድቁ ኖሯል። . ያምሃድ (የአሁኗ አሌፖ) ሰሜናዊ ሶርያን ለሁለት መቶ ዓመታት ተቆጣጥሮ ነበር፣ ምንም እንኳን ምስራቃዊ ሶርያ በ19ኛው እና በ18ኛው ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በብሉይ የአሦር መንግሥት በሻምሺ-አዳድ 1 አሞራውያን ሥርወ መንግሥት ይገዛ የነበረ ሲሆን እና በአሞራውያን በተመሰረተው የባቢሎን ግዛት ተያዘ። . ያምሃድ በማሪ ጽላቶች ውስጥ በምስራቅ አቅራቢያ ካሉት ኃያላን መንግስታት እና ከባቢሎን ሀሙራቢ የበለጠ ሎሌዎች እንዳሉት ተገልጿል ። ያምሃድ በአላላክ፣ ቃትና፣ በሁሪያን ግዛቶች እና በኤፍራጥስ ሸለቆ ላይ እስከ ባቢሎን ድንበር ድረስ ሥልጣኑን ሰጠ። የያምሃድ ጦር በኤላም (የአሁኗ ኢራን) ድንበር እስከ ዴር ድረስ ዘመቱ። ያምሃድ ከኤብላ ጋር በ 1600 ዓክልበ ገደማ በትንሿ እስያ በመጡ ኢንዶ-አውሮፓውያን ኬጢያውያን ድል ተደረገ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ, ሶርያ ለተለያዩ የውጭ ግዛቶች የጦር ሜዳ ሆናለች, እነዚህም የኬጢያውያን ኢምፓየር, ሚታኒ ኢምፓየር, የግብፅ ኢምፓየር, መካከለኛው የአሦር ኢምፓየር እና በትንሽ ደረጃ ባቢሎን ናቸው. ግብፃውያን በመጀመሪያ ደቡቡን፣ ኬጢያውያን፣ እና ሚታኒ፣ አብዛኛውን ሰሜናዊ ክፍል ተቆጣጠሩ። ይሁን እንጂ ከጊዜ በኋላ አሦር የበላይነቱን በማግኘቱ የሚታኒ ግዛትን በማጥፋት ቀደም ሲል በኬጢያውያንና በባቢሎን ተይዘው የነበረውን ሰፊ ​​ግዛት ያዘ። ከክርስቶስ ልደት በፊት በ14ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ፣ የተለያዩ ሴማዊ ህዝቦች በምስራቅ ከባቢሎንያ ጋር ያልተሳካ ግጭት ውስጥ የገቡት ከፊል ዘላኖች ሱታውያን እና የቀደምት አሞራውያንን የገዙ የምዕራብ ሴማዊ ተናጋሪ አራማውያን ነበሩ። እነሱም ለዘመናት በአሦርና በኬጢያውያን ተገዙ። ግብፃውያን ምዕራብ ሶርያን ለመቆጣጠር ከኬጢያውያን ጋር ተዋጉ; ጦርነቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰው በ1274 ዓክልበ ከካዴስ ጦርነት ጋር ነው። ምዕራቡም የኬጢያውያን ግዛት አካል ሆኖ እስከ ጥፋቱ ሐ. 1200 ዓክልበ.፣ ምስራቃዊ ሶርያ በአብዛኛው የመካከለኛው አሦር ግዛት አካል ሆኖ ሳለ፣ እሱም እንዲሁም በቴግላት-ፒሌሶር 1 1114-1076 ዓክልበ. የግዛት ዘመን አብዛኛውን ምዕራባዊ ክፍል ያጠቃለለ። ከክርስቶስ ልደት በፊት በ11ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በኬጢያውያን ጥፋት እና በአሦር ውድቀት፣ የአራም ነገዶች አብዛኛውን የውስጥ ክፍል ተቆጣጠሩ፣ እንደ ቢት ባሂያኒ፣ አራም-ደማስቆ፣ ሃማት፣ አራም-ረሆብ፣ አራም-ነሀራይም፣ የመሳሰሉ ግዛቶች መስራች እና ሉሁቲ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ክልሉ አራምያ ወይም አራም ተብሎ ይጠራ ነበር. በሰሜን መካከለኛ አራም (ሶሪያ) እና በደቡብ መካከለኛው በትንሿ እስያ (አሁኗ ቱርክ) ላይ ያተኮሩ በርካታ የሲሮ-ኬጢያ ግዛቶችን በመመሥረት በሴማዊ አራማውያን እና በህንድ-አውሮፓ ኬጢያውያን ቅሪቶች መካከል ውህደት ነበረ። ፣ ቀርኬሚሽ እና ሰማል።ፊንቄያውያን በመባል የሚታወቁት የከነዓናውያን ቡድን የሶሪያን የባህር ዳርቻዎች (እንዲሁም ሊባኖስ እና ሰሜናዊ ፍልስጤም) ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እንደ አምሪት፣ ሲሚራ፣ አርዋድ፣ ፓልቶስ፣ ራሚታ እና ሹክሲ የመሳሰሉ የከተማ ግዛቶችን ሊቆጣጠር መጣ። ከእነዚህ የባህር ዳርቻ ክልሎች በመላ በሜዲትራኒያን ባህር ውስጥ በማልታ ፣ በሲሲሊ ፣ በአይቤሪያ ባሕረ ገብ መሬት (በአሁኑ ስፔን እና ፖርቱጋል) እና በሰሜን አፍሪካ የባህር ዳርቻዎች እና በተለይም የካርቴጅ ዋና ከተማን መመስረትን ጨምሮ ተጽኖአቸውን በመላው ሜዲትራኒያን አሰራጭተዋል። በዘመናዊቷ ቱኒዚያ) ከክርስቶስ ልደት በፊት በ9ኛው ክፍለ ዘመን፣ እሱም ብዙ ቆይቶ የሮማን ኢምፓየር ተቀናቃኝ የትልቅ ግዛት ማዕከል ለመሆን ነበር። ሶሪያ እና የምስራቅ ምዕራባዊ አጋማሽ ከዚያም ወደ ሰፊው የኒዮ አሦር ግዛት ወደቀ (911 ዓክልበ - 605 ዓክልበ.)። አሦራውያን ኢምፔሪያል አራማይክን እንደ ግዛታቸው ቋንቋ አስተዋውቀዋል። ይህ ቋንቋ በ7ኛው እና በ8ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዓ.ም የአረቦች እስላማዊ ወረራ እስካበቃ ድረስ በሶሪያ እና በምስራቅ አካባቢ ሁሉ የበላይ ሆኖ እንዲቀጥል እና ለክርስትና መስፋፋት መሸጋገሪያ መሆን ነበረበት። አሦራውያን የሶሪያን እና የሊባኖስን ቅኝ ግዛቶች ኤቦር-ናሪ ብለው ሰየሙ። የአሦራውያን የበላይነት አብቅቷል አሦራውያን በተከታታይ ጨካኝ በሆኑ የውስጥ የእርስ በርስ ጦርነቶች ራሳቸውን ካዳከሙ በኋላ፣ ከሜዶን፣ ባቢሎናውያን፣ ከለዳውያን፣ ፋርሳውያን፣ እስኩቴሶች እና ሲሜሪያውያን ጥቃቶች ተከተሉ። በአሦር ውድቀት ወቅት እስኩቴሶች አብዛኛውን የሶርያን ክፍል ዘረፉ። የመጨረሻው የአሦር ጦር በ605 ዓክልበ. በሰሜን ሶርያ በቀርኬሚሽ ነበር። የአሦር መንግሥት በኒዮ-ባቢሎን ግዛት (605 ዓክልበ - 539 ዓክልበ.) ተከትሏል። በዚህ ወቅት፣ ሶርያ በባቢሎን እና በሌላ የቀድሞ የአሦር ቅኝ ግዛት በግብፅ መካከል የጦር ሜዳ ሆነች። ባቢሎናውያን እንደ አሦራውያን ግንኙነታቸው በግብፅ ላይ ድል ነሡ። ክላሲካል ጥንታዊነት የዛሬዋን ሶርያን ያቋቋሙት መሬቶች የኒዮ-ባቢሎንያ ኢምፓየር አካል ነበሩ እና በ 539 ዓክልበ በአካሜኒድ ኢምፓየር ተጠቃለለ፣ በታላቁ ቂሮስ የተመሰረተ። ፋርሳውያን ኢምፔሪያል አራማይክ ከአካሜኒድ ኢምፓየር (539 ዓክልበ - 330 ዓክልበ.) ዲፕሎማሲያዊ ቋንቋዎች እንደ አንዱ አድርገው ያዙ፣ እንዲሁም የአራም/ሶሪያ ኤበር-ናሪ አዲስ ባለ ሥልጣናት የአሦራውያን ስም ያዙ። ሶርያ በ330 ዓክልበ. በታላቁ እስክንድር ይገዛ በነበረው የግሪክ መቄዶንያ ኢምፓየር ተቆጣጠረች፣ እና በዚህም ምክንያት የኮኤሌ-ሶሪያ ግዛት የግሪክ ሴሌውሲድ ግዛት ሆነች (323 ከክርስቶስ ልደት በፊት - 64 ዓክልበ.)፣ የሴሌውሲድ ነገሥታት እራሳቸውን 'የሶሪያ ንጉሥ' ብለው እየለጠፉ ነበር። የአንጾኪያ ከተማ ዋና ከተማዋ ከ240 ጀምሮ ነው። ስለዚህም "ሶርያ" የሚለውን ስም ወደ ክልሉ ያስተዋወቁት ግሪኮች ናቸው። በመጀመሪያ በሰሜን ሜሶጶጣሚያ (ኢራቅ) የ"አሦር" የኢንዶ-አውሮፓ ሙስና ግሪኮች ይህንን ቃል አሦርን ብቻ ሳይሆን በምእራብ በኩል ያሉትን አገሮችም ለመግለጽ ተጠቀሙበት። ስለዚህ በግሪኮ-ሮማን ዓለም ሁለቱም የሶሪያ ሶርያ እና የሜሶጶጣሚያ አሦራውያን (የአሁኗ ኢራቅ) በምስራቅ "ሶሪያ" ወይም "ሶሪያውያን" ተብለው ተጠርተዋል ምንም እንኳን እነዚህ በራሳቸው የተለያየ ህዝቦች ቢሆኑም ግራ መጋባት ያጋጠመው ወደ ዘመናዊው ዓለም ይቀጥላል. በስተመጨረሻ የደቡባዊ ሴሉሲድ ሶሪያ አንዳንድ ክፍሎች በሄለናዊው ኢምፓየር ቀስ በቀስ መፍረስ ላይ በይሁዳ ሃስሞናውያን ተወሰዱ። ሶሪያ ከ 83 ዓክልበ. ለአጭር ጊዜ በአርሜኒያ ቁጥጥር ስር ወደቀች፣ በአርሜኒያ ንጉስ ታላቁ ቲግራኔስ ወረራ፣ በሶሪያ ህዝብ ከሴሉሲድ እና ከሮማውያን አዳኝ ሆኖ የተቀበለው። ነገር ግን የሮማ ኢምፓየር ጄኔራል የነበረው ታላቁ ፖምፔ ወደ ሶርያ በመሳፈር ዋና ከተማዋን አንጾኪያን በመያዝ በ64 ዓክልበ. ሶርያን የሮማ ግዛት አድርጐ በመቀየር ለሁለት አስርት ዓመታት የዘለቀውን የአርመን ግዛት መቆጣጠር አበቃ። ሶሪያ በሮማውያን አገዛዝ የበለፀገች ሲሆን በሀር መንገድ ላይ ስትራቴጅ በመገኘቷ ከፍተኛ ሀብትና ጥቅም ያስገኘላት ሲሆን ይህም ተቀናቃኞቹ ሮማውያን እና ፋርሳውያን የጦር አውድማ አደረጋት።ፓልሚራ, ሀብታም እና አንዳንድ ጊዜ ኃይለኛ ቤተኛ አራማይክ ተናጋሪ መንግሥት በሰሜን ሶርያ በ 2 ኛው ክፍለ ዘመን ውስጥ ተነሣ; ፓልሚሬኔ ከተማዋን በሮማን ግዛት ውስጥ ካሉት እጅግ ባለጸጋዎች መካከል አንዷ እንድትሆን የሚያደርግ የንግድ መረብ አቋቋመ። በመጨረሻ በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ የፓልሚሬኑ ንጉስ ኦዳኤናቱስ የፋርስን ንጉሠ ነገሥት ሻፑርን 1 አሸንፎ የሮማን ምሥራቅን ሙሉ በሙሉ ሲቆጣጠር የሱ ተከታይ እና መበለት ዘኖቢያ የፓልሚሬን ግዛት ሲመሠርት እሱም ግብፅን፣ ሶርያን፣ ፍልስጤምንን፣ አብዛኛው የእሢያ ክፍልን ለአጭር ጊዜ ድል አድርጓል። ትንሹ፣ ይሁዳ እና ሊባኖስ፣ በመጨረሻ በ273 ዓ.ም በሮማውያን ቁጥጥር ስር ከመውደዳቸው በፊት። ሰሜናዊው የሜሶጶጣሚያ አሦራውያን የአድያቤኔ መንግሥት በሮም ከመውረሯ በፊት ከ10 ዓ.ም እስከ 117 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በሰሜን ምስራቅ ሶርያ ያሉትን ቦታዎች ተቆጣጠረ። የአረማይክ ቋንቋ በጥንቷ ብሪታንያ ውስጥ እስከ ሃድሪያን ግንብ ድረስ ርቆ ይገኛል፣ በፎርት አርቢያ ቦታ በፓልሚሬን ስደተኛ የተጻፈ ጽሑፍ ጋር። በመጨረሻ የሶሪያ ቁጥጥር ከሮማውያን ወደ ባይዛንታይን ተሻገረ፣ በሮም ግዛት መከፋፈል። የባይዛንታይን ግዛት በነበረበት ወቅት በብዛት ኦሮምኛ ተናጋሪ የነበረው የሶሪያ ሕዝብ ምናልባት እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ እንደገና ሊበልጥ አልቻለም። ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ7ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የአረብ እስላማዊ ወረራ ከመጀመሩ በፊት አብዛኛው ህዝብ አራማውያን ነበሩ፣ ነገር ግን ሶርያ የግሪክ እና የሮማውያን ገዥ መደቦች መኖሪያ ነበረች፣ አሦራውያን አሁንም በሰሜን ምስራቅ፣ በባሕር ዳርቻዎች ያሉት ፊንቄያውያን፣ የአይሁድ እና የአርመን ማህበረሰቦች ይኖራሉ። በደቡብ ሶሪያ በረሃዎች ውስጥ ናባቲዎች እና ቅድመ-እስልምና አረቦች እንደ ላክሚድስ እና ጋሳኒድስ ባሉ ትላልቅ ከተሞች ውስጥ ነበሩ ። ምንም እንኳን ሌሎች አሁንም ይሁዲነት፣ ሚትራይዝም፣ ማኒቺኒዝም፣ ግሪኮ-ሮማን ሃይማኖት፣ የከነዓናውያን ሃይማኖት እና የሜሶጶጣሚያ ሃይማኖት ቢከተሉም የሶርያ ክርስትና እንደ ዋና ሃይማኖት ያዘ። የሶሪያ ትልቅ እና የበለፀገ ህዝብ ሶሪያን ከሮማውያን እና የባይዛንታይን ግዛቶች በተለይም በ 2 ኛው እና በ 3 ኛው ክፍለ ዘመን (እ.ኤ.አ.) በጣም አስፈላጊ ከሆኑት መካከል አንዷ አድርጓታል።በሴቨራን ሥርወ መንግሥት ጊዜ ሶሪያውያን ከፍተኛ መጠን ያለው ሥልጣን ያዙ። የሮም ቤተሰብ እና እቴጌይቱን የንጉሠ ነገሥት ሴፕቲሚየስ ሴቭረስ ሚስት በመሆን ያገለገሉት ጁሊያ ዶምና ከኤሜሳ ከተማ (የአሁኗ ሆምስ) ከተማ የሆነች ሶሪያዊት ስትሆን ቤተሰቧ የኤል-ጋባል አምላክ የክህነት መብት የነበራቸው ናቸው። ታላላቅ የወንድሟ ልጆች፣ እንዲሁም ከሶሪያ የመጡ አረቦች፣ እንዲሁም የሮማ ንጉሠ ነገሥት ይሆናሉ፣ የመጀመሪያው ኤላጋባልስ እና ሁለተኛው የአጎቱ ልጅ አሌክሳንደር ሴቨረስ ነው። ሌላው የሮም ንጉሠ ነገሥት የሶሪያዊው አረብ ፊልጶስ (ማርከስ ጁሊየስ ፊሊጶስ) ሲሆን የተወለደው በሮም አረቢያ ነው። ከ 244 እስከ 249 ንጉሠ ነገሥት ነበር እና በሦስተኛው ክፍለ ዘመን ቀውስ ውስጥ ለአጭር ጊዜ ገዛ። በንግሥና ዘመኑ፣ በትውልድ ከተማው ፊሊጶፖሊስ (በአሁኑ ሻህባ) ላይ ያተኮረ ሲሆን ከተማዋን ለማሻሻል ብዙ ግንባታዎችን የጀመረ ሲሆን አብዛኞቹ ከሞቱ በኋላ ቆመዋል። ሶሪያ በክርስትና ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ አለች; ሐዋርያው ​​ጳውሎስ በመባል የሚታወቀው የጠርሴሱ ሳውሎስ ወደ ደማስቆ መንገድ ተለውጦ በጥንቷ ሶርያ በምትገኘው አንጾኪያ በምትገኘው የክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትልቅ ሰው ሆኖ ብቅ አለ፣ በዚያም በብዙ የሚስዮናውያን ጉዞዎች ላይ ወጣ። ( የሐዋርያት ሥራ 9:1–43) መካከለኛ ዘመን መሐመድ ከሶሪያ ሕዝብና ጎሣዎች ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ያደረገው ግንኙነት በጁላይ 626 በዱማቱል ጃንዳል ወረራ ወቅት ተከታዮቹ ዱማን እንዲወርሩ ትእዛዝ አስተላልፏል።ምክንያቱም መሐመድ አንዳንድ ጎሳዎች በሀይዌይ ዘረፋ ላይ ተሰማርተው መዲናን ራሷን ለመውጋት መዘጋጀታቸውን መረጃ ስለደረሰበት ነው። ዊልያም ሞንትጎመሪ ዋት ይህ በጊዜው መሐመድ ያዘዘው ታላቅ ጉዞ ነበር ይላሉ፣ ምንም እንኳን በዋና ምንጮች ላይ ብዙም ማስታወቂያ ባይሰጠውም። ዱማት አል-ጃንዳል ከመዲና 800 ኪሎ ሜትር (500 ማይል) ይርቅ ነበር፣ እና ዋት ወደ ሶሪያ የሚያደርገዉ ግንኙነት እና ወደ መዲና የሚደርሰዉ ነገር ከመቋረጡ በቀር ለመሐመድ ምንም አይነት ፈጣን ስጋት እንደሌለ ተናግሯል። ዋት "መሐመድ ከሞቱ በኋላ ስለተደረገው መስፋፋት አንድ ነገር አስቀድሞ እየገመተ ነው ብሎ ማሰብ አጓጊ ነው" እና የወታደሮቹ ፈጣን ጉዞ "የሰሙትን ሁሉ ያስደነቀ" መሆን አለበት። ዊልያም ሙር መሐመድ ተከትሎ 1000 ሰዎች በሶሪያ ግዛት ሲደርሱ የሩቅ ጎሳዎች ስሙን ባወቁበት ወቅት የመሐመድ የፖለቲካ አድማስ ሲራዘም ጉዞው ጠቃሚ ነበር ብሎ ያምናል።በ640 ዓ.ም ሶሪያን በካሊድ ኢብኑል ወሊድ የሚመራው የአረብ ራሺዱን ጦር ተቆጣጠረች። በ 7 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ የኡማያ ሥርወ መንግሥት የዚያን ጊዜ የግዛቱ ገዥዎች የግዛቱን ዋና ከተማ በደማስቆ አስቀመጠ። በኋለኛው የኡመያድ አገዛዝ ወቅት የሀገሪቱ ሥልጣን ቀንሷል; ይህ በዋነኛነት በጠቅላይ አገዛዝ፣ በሙስና እና በተፈጠሩት አብዮቶች ምክንያት ነው። ከዚያም የኡመውያ ሥርወ መንግሥት በ750 በአባሲድ ሥርወ መንግሥት ተወግዶ የግዛቱን ዋና ከተማ ወደ ባግዳድ አዛወረው። አረብኛ - በኡመያድ አገዛዝ ውስጥ ይፋ የሆነው - በባይዛንታይን ዘመን የነበረውን ግሪክ እና አራማይክ በመተካ ዋና ቋንቋ ሆነ። እ.ኤ.አ. በ 887 በግብፅ ላይ የነበሩት ቱሉኒዶች ሶሪያን ከአባሲዶች ወሰዱት ፣ እና በኋላ አንድ ጊዜ በግብፅ ኢክሺዲዶች እና አሁንም በሃምዳኒዶች በሰይፍ አል-ዳውላ በተመሰረተው አሌፖ ተተኩ ።
51189
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8C%A2%E1%8B%AB%20%E1%89%B5%E1%8A%AD%E1%88%8D%20%E1%8B%B5%E1%8A%95%E1%8C%8B%E1%8B%AD
የጢያ ትክል ድንጋይ
የጢያ ትክል ድንጋይ የጢያ ትክል ድንጋይ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በጉራጌ ዞን በተለይም ከአዲስ አበባ ወደ ቡታጂራ በሚወስደው መንገድ 88 ኪሎ ሜትር ርቃ ከምትገኘው ሶዶ ወረዳ በጥያ ከተማ ይገኛል፡፡ ጢያ በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጧ ከምድር ሰቅ (ኢክዌተር) 8026′ ሰሜን 38037′ ምሥራቅ እንደሆነ የዩኔስኮ ዘገባዎች ያመለክታሉ፡፡ የጢያ ታሪካዊ ድንጋይ በቁጥር 44 የሚደርሱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 32 ያህሉ ልዩ ልዩ ቅርጾች ምስሎች ያሉባቸው ናቸው፡፡ ሁሉም ድንጋዮች የተለያየ ርዝመት፣ ስፋትና ውፍረት አላቸው፡፡ ይሁንና በሌሎቹ ሥፍራዎች ማለትም በአገር ውስጥ በስልጢ ወይም በግብፅ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በሩቅ ምሥራቅ፣ በአውሮፓና በላቲን አሜሪካ እንደምናያቸው የመቃብር ድንጋዮች አንድም አራት ማዕዘን ወይም ድቡልቡል አይደሉም፡፡ በአብዛኛው ከታች ሰፋ ብለው ወደ ላይ እየሾጠጡ የሚሄዱ ናቸው፡፡ የአንዳንዶቹ ትክል ድንጋዮች ቁመትም ከ1-5 ሜትር ሊረዝም እንደሚችል የአርኪዮሎጂ አጥኚዎች ሥራዎች ያመለክታሉ፡፡ በድንጋዮቹ ላይ የተቀረጹት ምስሎችም የጎራዴ ወይም የሰይፍ ወይም የጩቤ፣ የጦር፣ የትራስ እንጨት፣ ክብ ዳቦ ወይም ፀሐይ መሰል ቅርጾች፣ የግማሽ ጨረቃ ምስሎች እጆቹን ወደላይ የዘረጋ ሰው ክንዶች ናቸው፡፡ በቅድመ ታሪክ ይኖሩ የነበሩት ኢትዮጵያውያን ድንጋዮቹን ለምን እንደተከሏቸው ባይታወቅም ትልቅ የጦር መሪዎች፣ ገዥዎችና ታላላቅ ሰዎች የተቀበሩባቸው ሥፍራዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገመታል፡፡ ሊቃውንቱ ይህን ግምት የወሰዱት በአሁኑ ጊዜ በሶዶ፣ በስልጢና በጌድኦ ካሉት የመቃብር ድንጋዮች እንደሆነም ያስረዳሉ፡፡ ምንም እንኳን ትክል ድንጋዮቹ መች እንደተተከሉ በትክክል ማወቅ ባይቻልም አንዳንድ አጥኝዎች ከ800 ዓመት በፊት እንደተተከሉ ይገምታሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ከቅድመ ታሪክ በፊት የነበሩ ኢትዮጵያውያን የተሠሩ ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገምታሉ፡፡ የተወሰኑ ትክል ድንጋዮቹ ለብዙ ዓመት ሳይወድቁ የቀሩበትን ምክንያት ሲያብራሩም ከመሬት በታች ስምንት ሜትር ርዝመት ስላላቸው እንደሆነ ይገልጣሉ፡፡ በድንጋዮቹ ላይ ያለው የሰይፍ ብዛት ሟች ምን ያህል ልጆች እንዳሉት እና ምን ያህል አውሬ እንደገደለ ያሳያሉ፡፡ የጢያ ትክል ድንጋይ የአውሮፓውያንን ዓይን መሳብ ከጀመረ ብዙ ዓመትን ያስቆጠረ ሲሆን ኢጣሊያውያን የአርኪዮሎጂ ባለሙያዎች ጥልቅ ጥናት ባያካሂዱም ከ70 ዓመት በፊት ኢትዮጵያን ወርራ በነበረችበት ጊዜ የመጡ ተመራማሪዎች ስለድንጋዮቹ መኖር ዘግበዋል፡፡ የዛሬ 84 ዓመት ወደኢትዮጵያ መጥቶ የነበረው ጀርመናዊ አጥኚም በዚህ ሥፍራ በኩል አልፎ እንደነበረና የጎራዴ ምስል ያላቸው የድንጋይ ትክሎች እንዳየ በጥናቱ አመልክቷል፡፡ ከዚህ አጥኚ ቀደም ሲልም ኑቪለ እና ፔር ዛይስ የተባሉ አውሮፓውያን ጥያን መጎብኘታቸውን የዩኔስኮ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ ትራቭል አፍሪካ በተሰኘው የጎብኝዎች የኢንተርኔት መረጃ ምንጭም ጢያ የሚገኙት ትክል ድንጋዮች አዳዲ ማርያም ከተባለው ከድንጋይ ፍልፍል የተሠራው ቤተ ክርስቲያን፣ ሀረ ሸይጣን ከተባለው ክሬተር ሐይቅ፣ ከመልካ አዋሽ መስመር ጋር ስለሚገኙ ለጎብኝዎች በአንድ ጉዞ ብዙ ታሪካዊ ቦታዎችን ለመጎብኘት ያስችለዋል በማለት አስፍሯል፡፡ ፊሊፕ በሪግ የተሰኙት አጥኚም የጥያ ትክል ድንጋይ ጥንታዊነትን ለዓለም በማስተዋወቅ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው ይታወቃል፡፡ የፈረንሳይ አርኪዮሎጂ ባለሙያዎች መረጃ እንደሚያመለክተው የጢያ ትክል ድንጋይ ባለበት ቦታ ዕድሜያቸው ከ18-30 የሚገመቱ ብዙ ወጣቶች በአንድ ላይ የተቀበሩበት ሥፍራ ነው፡፡ የፈረንሳይ ሊቃውንት እንደሚሉት ሥፍራው የመቃብር ቦታ ከሆነ ከዓለም የመቃብር ሥፍራዎች አኳያ የምንመለከተው ይሆናል፡፡ በኦክስፎርድ ጁኔር ኢንሳይክሎፒዲያ (ቅጽ 12፡1957) ‹‹ቱምስ›› () በሚል ርዕስ ሰፍሮ እንደምናገኘው ደግሞ በጥንታዊት ግሪክ ሦስት ዓይነት የመቃብር ዓይነቶች ነበሩ፡፡ እነሱም ‹‹ስቴል››፣ ‹‹ሙስሊየም››እና ‹‹ሳርኮፋገስ›› የሚባሉት ናቸው፡፡ ‹‹ስቴል›› የሚባለው የመቃብር ዓይነት የሟቹ ምስል ቁም ለቁም የተቀረጸበት ወይም የቤተሰቡ አጠቃላይ ሁኔታ የሚያመለክት ድንጋይ ተቀርጾ የሚተከልበት ሲሆን ይህም ከክርስቶስ ልደት በፊት ከስድስተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበረ ነው፡፡ ትራቭል አፍሪካ የተሰኘው መጽሐፍ እንደሚያወሳው ከጥያ ጋር የሚመሳሰሉ ትክል ድንጋዮች በሶዶ ወረዳ 160 ሥፍራዎች ሲኖሩ ከነዚህም ድንጋዮች በኢማም አሕመድ ኢብራሂም (አሕመድ ግራኝ) እንደተተከሉ በአፈ ታሪክ ቢነገርም በትክክል ማን እንደተከላቸው ግን አይታወቅም፡፡ የአርኪዮሎጂ አጥኚዎች እንደሚሉት የጢያ ትክል ድንጋዮች ከሰሐራ በታች ካሉ ትክል ድንጋዮች ከአክሱም በስተቀር በዕድሜ የሚበልጣቸው የለም፡፡ ከላይ የተጠቀሱትን ምክንያቶች መሠረት በማድረግ ቦታው እ.ኤ.አ ከ1980 ጀምሮ በዓለም የቅርስ መዝገብ ሰፍሮ ይገኛል፡፡
51245
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8C%AD%E1%88%AD%20%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%88%9B%E1%88%AB%20%E1%88%9B%E1%89%B3%E1%8C%88%E1%8B%AB%20%E1%88%80%E1%88%B3%E1%89%A5
አጭር የአማራ ማታገያ ሀሳብ
አማራ….. ምን ከማን ከየት ወዴት ለምን እንዴት? .........በአገናኝ ከበደ ከሁሉም ማስተዋል ይቅደም በ1960ዎቹ የስልጣን ጥመኝነት ጥላቻ የቅኝ ገዥ ፍላጎት አስፈፃሚ የኢትዮጵያን የወቅቱን የፖለቲካ አሰላለፍ ያልተረዱ የተዘበራረቀ የፖለቲካ አላማ ያላቸው እና በስሜት ያበዱ እንደነ ኦነግ ሕዋሓት መኢሶን እና ኢህአፓ የመሳሰሉት የፖለቲካ ሀይሎች የነበሩበት ወቅት ነዉ፡፡ የገባዉም ያልገባዉም የመገንጠል ፍላጎት ያለዉም የሌለዉም ከዉጭ ጠላት የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለትም የማይደረግለትም በአንድ ላይ ጃንሆይ ላይ ተነሱ፡፡ ግራ የገባቸው ቅኑ ንጉስ ማስተዳደር ከቻላችሁ ዙፋኑ ይሄው ብለው ስልጣናቸውን ለቀቁ፡፡ አለቀ!!! የመንጋ ፖለቲካ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያን ሽባ አደረጋት!!! ንጉሱ ከስልጣን ወረዱ!!! የስልጣን ጥመኛ የሆነ ሀይል በያዘው አፈሙዝ እነ መኢሶንን እያሰፈራራ ስልጣን ላይ ቁብ አለ፡፡ ዲፕሎማቶች ሚኒስተሮች እና የጦር ጀኔራሎች ተረሸኑ፡፡ ይሄዉ የፖለቲካ ብስለት የሌለዉ ሀይል የኢትዮጵያን እንቁ ልጆች መቁረጥ ጀመረ፡፡ መንጋዉም ተፀፀተ እንደገና ደርግን አወገዘ ግን አሁንም መንገዉ ላይ የጥይት ናዳ ወረደ፡፡ ከዚህ ላይ ብዙ ትዉልድ አለቀ፡፡ ይህን ሁሉ የወለደው አለማስተዋል እና ሰሜት ያነገበ የመንጋ ፖለቲካ ነው፡፡ ሁሉም ከንጉሱ በኋላ የተሻለ መንግስት መጥቶ የተሻለ ሂወት የሚቀጥል መስሎት ነበር፡፡ ነበር ነው፤ ግን አልሆነም፡፡ ከአፄ ሐይለ ሥላሴ በኋላ ሀገር የሚያስተዳደር ብቁ ሀይል አልነበረም፡፡ ሁሉም ሀገሪቱ እና ህዝቡ በማያውቁት የሶሻሊዝም የፖለቲካ መጠጥ ሰክሯል የሀገሩን ፖለቲካ መረዳት ከብዶታል፡፡ደርጉ ደግሞ መልክህ አላማረኝም በማለት የሰከረዉንም ያልሰከረውንም ይረሽናል፡፡ ከጥይት ቀላ የተረፈው ትዉልድ የደርጉ ደካማ ያገር ዉስጥ እና የሀገር ዉጭ ፖለቲካ ለፈጠረው እሳት ማገዶ ሆነ፡፡ በመጨረሻም ባልተጠበቀ መንገድ የፖለቲካ ብስለት የሌለዉ ወታደራዊ ሀይል ህዝቡን እንዳሰቃየ ሕዋሓት በሚባል ሌላ የኢምፐሪያሎች ባሪያ የሆነ ባንዳ የፖለቲካ ስርዓት ተተካ፡፡ የሀገሪቱ እና የህዝብም ስቃይ ለ 27 ዓመታት ቀጠለ፡፡ በተለይ ይህ ማፊያ የፖለቲካ ድርጅት አማራ-ጥል ማኒፌስቶ እና ህገ-መንግስት ከማዘጋጀት እስከ አማራ የዘር ጭፍጨፋ የደረሰ ኢ-ህጋዊ ኢ-ሰባዊ እና ኢ-ሞራላዊ ስራ በመስራት የነጭ አለቆችን አስደሰተ፡፡ ኋላም ቁጭት በወለደው መራር የአማራ ትግል ለመቀበር በቃ!!! በመጨረሻም እኔም የዉስጥ ትግል አደርጌአለሁ የሚል ከዚያው ከህዋሓት የወጣ ግን በህዋሓት አስተምሮ ያደገ በምስራቅ አፍሪቃ ሉአላዊ የሆነች ኦሮሚያ የምትባል ሀገር በአጭር ጊዜ መመስረት ያሰበ የካቢኔ ስብስብ ብልፅግና በሚል ስያሜ ስልጣኑን ያዘ፣ ስልጣኑን በያዘ ንጋት ከፍተኛ ድጋፍ ያገኘዉ ከአማራ ህዝብ በኩል ነበር፤ ግን በማግስቱ አማራ የለመደውን ሞት ባለመደው ሰይጣን መጎንጨት ጀመረ! የአማራ ስቃይ መቆም አልቻለም! ጭራሽ የዚህ የፖለቲካ አመራሮች አማራ ጠሎችን በማሰባሰብ በአደባባይ አማራ ላይ የዘር ፍጅት አውጀው አማራዉን ማሰገደል ቀጠሉ….. ወዳጀ በ1960ዎቹ የተፈጠረች አለማስተዋል ይህን ሁሉ መከራ ወለደች!!! እስቲ እያስታዋልን!! 1. መግቢያ ወደ ዋናዉ ፅሁፍ ከመግባታችን በፊት በወፍ በረር የ አምሓራ ምንነትን ከስረወቃላዊ ነገዳዊ እና ብሄራዊ ትንታኔ ጋር አያይዘን እንመለከታለን፡፡ ከስረወ-ቃል አኳያ አምሓራ ማን ነዉ የሚለዉን በተመለከተ የአለቃ ታየ ገብረ-ማሪያምን አና የአቶ አጽሜን ሀሰብ ጨምቆ መመልከቱ ጥሩ ነዉ፡፡፡ሙህራኑ አምሓራ የሚለዉ ቃል ከእብራይስጥ ሂሜያርት ከሚባል ቃል እና ከግዝ አም-ሓራ ከሚባል ቃል ሊመጣ እንደሚችል ግምታቸዉን ከአስቀምጡ በኋላ አምሓራ የሚለዉን ቃል ጨዋ ሀያል ህዝብ እና ነፃ ህዝብ በማለት ይተነትኑታል(ታየ፣1898)፡፡ ዓስራት የአለቃ ታየን የኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ መፅሀፍ እና የመራሪስ አማንን መፅሀፈ ኢብርሐት አጣቅሶ እንደፃፈዉ የአምሓራ ነገዳዊ የዘር ግንደ ከሴም ግንድ ከሆነው አርፋክሳድ የሚመዘዝ ነዉ፡፡ አምሓራ ሴማዊ ህዝብ ነዉ፡፡ ሌላዉ የአምሓራ የብሄር ማንነት ጉዳይ ነዉ፡፡ አዲስ አበባ ዪኒቨርሰቲ የአማራኛ መዝገበ ቃላት በሚል ርዕስ ባሳተመዉ መፅሀፉ ብሄርን አንድ አይነት ባህል እና ስነ-ልቦናዊ አመለካከት ያለዉ በታሪክ እና በኢኮኖሚ የተሳሰረ ህዝብ በማለት ይገልፀዋል፡፡ አንቶኒ ሰሚዝ የሚባል ሙህር በ2001 እ.ኤ.አ በፃፈዉ የብሄር ማንነት አተረጓጎም በሚለዉ መፅሀፉ ብሄር ማለት በባህል እሳቤ በትዉስታ በቋንቋ በዘር ግንድ እና በታሪክ አንድ የሆነ የማህበረሰብ ስብስብ ነዉ ይላል፡፡፡ አምሓራ ከላይ በተጠቀሱት የብሄር ትርጓሜ ሚዛን ሲታይ ብሄር ነዉ፡፡ በሁሉም አቅጣጫ የሚኖር አምሓራ ተመሳሳይ ባህል አለዉ አንድ የሚያደረገዉም የታሪክ ገድል አለዉ፤ ተመሳሳይ ስነልቦናዊ ስሪትም አለዉ፤ ከዚህም በተጨማሪ የራሱ የዘር ግንድ አለዉ!!!! ሁኖም አንዳንድ በበታችነት ስሜት የተጠቁ በአምሓራ መሰዋት ኢትዮጵያን ማቆየት የሚሹ እንዲሁም ሌሎች ትናንሽ ሉአላዊ ሀገራትን መፍጠር የሚፈለጉ የኢምፐሪያሊስት ባሪያዎች የ1960 ፀረ- አምሓራ ሙህራን ፀረ-አምሓራ-ኢትዮጵያዊ ፖለቲከኞች እና ድንዙዝ ተከታዮቻቸዉ አምሓራን ከሀይማኖት ከቋንቋ እና ከኢትዮጵያዊነት ጋር በማላተም እንዲሁም የአምሓራ መኖሪያ የሆኑ የወሎ የሽዋ የጎጃም እና የጎንደር ክፍለ-ሀገራትን እንደማንነት በመቁጠር አምሓራ የሚባል ማንነት የለም ይላሉ፡፡ ፀረ- አምሓራ ሙህራኖች አምሓራን በስሜን ኢትዮጵያ ብቻ በተለያዩ አከባቢወች የሚኖር የአማረኛ ቋንቋ ተናጋሪ እና የኦርቶዶክስ ሀይመኖት ተከታይ የሆነ ማህበረሰብ ይሉታል(ዓስራት፣2008 እና ይሁኔ፣2010)፡፡ፀረ-አፍሪቃ ፀረ-ኢትዮጵያ እና አውሮፓ አፍቃሪ ፖለቲከኞች የግል ጥቅማቸዉን ለማስጠበቅ ስልጣን ለመያዝ የኢትዮጵያን ሀብት ለመመንዘር እና ኢትዮጵያን ለማፍረስ ኢትዮጵያን እየጠበቀ ያለዉን አምሓራ ማዳከም ስላለባቸዉ አምሓራ ጨቆኝ ሌላዉ ተጨቋኝ ነበር የሚል ትርከት ፈጥረዉ ይታያሉ(ግርማ፣2008)፡፡ ይህ ለዘመናት የቆየ ኢ-ተገቢያዊ ፀረ-አምሓራ እና ፀረ-ኢትዮጵያ ሴራ በአንድ በኩል አምሓራ ግላዊ ባህሪ አንዲያዳብር እና በህልዉናዉ ላይ የተጋረጠበትን አደጋ እንደ ብሄር አንድ ሁኖ እንዳይመክት ትልቅ እንቅፋት ሁኖ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል በኢትዮጵያ የተለያየ ክፍል ያሉ ብሄሮች አምሓራን ጠላት እና ገፊ አድረገዉ አምሓራዉ ላይ እሰር እና ግድያ እእዲፈጽሙ መንገድ የከፈተ ነዉ፡፡ ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሀል() እንደሚባለዉ ከአስራ ስድስተኛዉ ክፍለ ዘመን ጀምሮ አምሓራ በኦሮሞ እና በአዳል ሱልጣኖች መሳደዱ ሳያንሰዉ፤ እንዲሁም ለባለፉት አመታት በአባገነናዊ የደርግ ስርዓት እንዲሁም በትህነግ አስተዳደር የደረሰበት የግፍ ጠባሳ ገና ሳይደርቅ ጭራሽ በግልባጭ ለባለፉት ችግሮች ሁሉ አምሃራ ተጠያቂ ሁኗል፡፡ ስለዚህ አምሓራዉ አንድነቱን አጠነክሮ እና ህለዉናዉን አረጋግጦ እራሱን ያድን ዘንድ እና ኢትዮጵያን ያቆይ ዘንድ የአምሓራ መደራጀት ብሄርተኝነት እና ህልዉናን የማቆየት አስፈላጊነት ላይ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ ነዉ፡፡ 2. ነፍጥ የአማራ የሰላም ምንጭ ከአፍሪቃይቱ አልጀሪያ የሚገኘዉ የመካከለኘዉ ክፍለ ዘመን የፖለቲካ የፍልስፍና እና የሀይማኖት ሰዉ ቅዱስ ኦግሰቲን ሰላም ዳቦ አይደለም ይልሃል፡፡ አንድ ዳቦ ለአንተ በቂ ብቻ ሳይሆን ሊበዛብህም ይችላል፡፡ ወደ ዳቦ ቤት ጎራ ብለህ አንድ ዳቦ ገዝተህ ለብቻህ ስትበለዉ ለራስህ ብዙ እና በቂ ሁኖ እራብህን ሊመክትለህ ይችላል፡፡ ሁኖም የገዛኸዉን ዳቦ ወደ አፍህ ከመድረሱ በፊት ለሌላ ሰዎች ስታከፋፍለዉ ደግሞ ያንተን ድረሻ ጨምሮ ለሁላችሁ የሚታደለዉ የዳቦ መጠን ትንሽ ነዉ፡፡ ሰላም ግን ከዚህ በተቃራኒዉ ነዉ፡፡ ሰላምን ከሁሉም ጋር ስትካፈል የሰላም መጠኑ ቢበዛ እንጅ አያንስም፤ አንተም ብትሆን ሰላምህ ይበዛልሃል፡፡ ግን የኦሮሞ ፖለቲከኞች እኔ ብቻ ሰላም ከሆንኩ ሌላዉ የራሱ ጉዳይ ለሌሎችም ቢሆን ሰላምን አላካፍልም፤ ሰላምንም ሌሎች እንዳያገኙ እከለክላለሁ በማለት ነጋ ጠባ ካገኙት ጋር መናከስ ይዘዋል:: በተለይ ደግሞ ይህ ጉዳይ በማንነት አማራ በሆኑ እና አማረኛ ተናጋሪ በሆኑ ህዝቦች ይጠነክራል፡፡ አብይ እና የድብቅ እቅድ አስፈፃሚ ቡድናቸው አዲስ አበባን እና ወሎን አካታ የምትይዝ ሌላዋን የምስራቅ አፍሪቃ ሀገር ለለመስረት መንገድ ጠረጋው የተሳከ ይሆን ዘንድ የትኘውም አካባቢ የሚኖር የአማራ ተወላጅ ሆን ተብሎ በኢኮኖሚ እና በፖለቲካ እንዲዳከም ተደርጓል:: አምሓራዉስ ቢሆን እነሱ ማጋራት ያልፈለጉትን ሰላም ብቻዉን ለምን ይፈልገፋል!!! አምሓራ የራሱን ሰላም መፈለግ አለመት፤ ሰላሙ ነፍጡ ነው፡፡ 3. ዉክልና ለባለፉት ሀያ ሰባት ሲደመር አምስት ዓመታት አማራ በኢትዮጵያ ህገ-መንግስት የፖለቲካ ይሁን የኢኮኖሚ ተቋም ተወክሎ አያዉቅም፤ በማንነቱ ተገሏል ተዘልፏል እንዲሁም ተሰዷል፡፡ ቻርለስ ቴለር የሚባል የፖለቲካ ሙህር በሚታወቅበት “” ፅሁፉ አንድ አካል ዉክልና አጣ የሚሉት እዉነት በዚያ አካል ላይ የተሰራ የታሪክ መዛባትን የሀሰት ታሪክ ትርከትን እና ስም ማጥፋትንም ጭምር ያካትታል ብሎ ተንትኖ ባስቀመጠው ፅሁፍ መሰረት የአማራን ሁኔታ ስናይ አማራ በኢትዮጵየያ ዉስጥ በሁሉም ዘርፎች ዜሮ ዉክልና አለው:: 4. አምሓራዉ ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች 4.1. የበላይነተን ሱስ የማስቀጠል ፖለቲካ ( ይህ የፖለቲካ አካሄድ በህዋሓት ሰዎች እየተተገበረ ሲሆን አሁንም የኦሮሞ ፖለቲከኞች በብልፅግና ስም የኢትዮጵያን ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ በመቆጣጠር የበላይ ሁነዉ መኖር የሚፈልጉበት አካሄድ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በኦሮሞ ፖለቲከኞች እና ኢሊቶች ጭምር ኦሮሙማ የሚባል ፕሮጀክት በመቅረጥ የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦች የመሰልቀጥ ተግባር ስራ ላይ ነው፡፡ ኦሮሙማ የሴምን ፖለቲካ ማጥፋት እና ሀበሻን ማጥፋት ሌላ አጀንዳው ሲሆን፤ በዚህ ፕሮጀክት ኤርትራዎች ጭምር የኦሮሙማ ኢላማ ናቸው፡፡ ኦሮሙማ የምስራቅ አፍሪካን ፖለቲካ ያፈርስ ዘንድ እና ሴምን ያጠፋ ዘንድ ጠንካራዉን የአማሃራን ህዝብ እና ክልልን ያገለለ ኢፍታዊ የስልጣን ክፍፍል እንዲሁም በተለየ መልኩ ኢፍታዊ የሆነዉ የኢኮኖሚ እና የሀብት ስርጭትን ያደርጋል፡፡ በአጠቃላይ የበላይነተን ሱስ የማስቀጠል ፖለቲካ () ከህዋሓት ወደ ኦሮሞ ከዚህ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ 4.2. ጠቅላይ ሚንስተር አብይ አህመድ ወሳኝ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መዋቅር ቦታዎችን ለኦሮሞ ብልፅግና አባላት እና ለኦነግ አመራሮች እየሰጡ ይገኛሉ(አንዳንዶቹም ኦሮሞ በመሆናቸዉ ብቻ ገና ከዩኒቨርስቲ እንደተመረቁ ካለምንም ልምድ የትልቅ ፐሮጀክት አላፊ ሁነዋል)፡፡ 4.3. የኢኮኖሚ አሻጥር ኢፍታዊ የሀብት እና የኢኮኖሚ ክፍፍሉ እንደቀጠለ ነዉ!!!! ለምሳሌ በህዝብ ቁጥር ከኦሮሞ የተሻለው እና ከፍተኛ ግብር የሚሰበሰብበት የአማሃራ ህዝብ ለ2012 ዓ.ም የተመደበለት በጀት 10 ሚሊዮን ከማይሞላው ከትግራይ ህዝብ ያነሰ ነዉ፡፡ ለ 50 ሚሊዮን አማራ ተመጥኖ የተሰጠዉ የ2012 ዓ.ም በጀት ከሁልም ያነሰ ነዉ! የአማራ ባለሃብት የሚገብረዉን ስንመለከት በኢትጵያ ከፍተኛ ግብር የሚሰበሰበው ከአማራ ባለሀብት ሲሆን ከግብር በሚገኘው ገቢ ኦሮሞ ይለማበታል፡፡ ለምሳሌ የ2012 ዓ.ም የበጀት ድልድል እንደሚከተው ቀርቧል ሀ. የአማራ ክልል በጀት – 47.4 ቢሊዮን ብር ለ. የአዲስ አበባ ከተማ በጀት — 48.7 ቢሊዮን ብር ሐ. የትግራይ ክልል በጀት50 ቢሊዮን ብር መ. የኦሮሚያ ክልል በጀት – 70.1 ቢሊዮን ብር 4.4. ተተኳሽ ሚሳኤሎች ትላልቅ የፋብሪቃ ፓርኮች እና ግዙፍ ፐሮጅክቶች ከትግራይ ክልል ወደ ኦሮሚያ ክልል መዞር ከጀመሩ ቆይተዋል፡፡ በተለይ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት እና በህዋሓት አማፅያን ጦርነት በተካሄደበት ወቅት የተለያዩ አስፈላጊ አላቂ ቁሶች ወደ ኦሮሚያ ክልል እንዲሸሹ ተደርገዋል፡፡ 4.5. ወሳኝ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች ሁሉም ማለት በሚቻል ደረጃ ኦሮሞ ናቸው፡፡ 4.6. የገንዘብ የገቢ የጉምርክ የባንክ እና የደህንነት ቦታወች በጥንፈኛ ኦሮሞ ኢሊቶች ተሞልተዋል፡፡ 4.7. አማራ በክልሉ ውስጥ እና ከክልሉ ውጭ ተረጋግቶ ንቁ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተሳትፎ እንዳያደርግ እረፍት መንሳት፤ ይህ በየጊዜው የሚፈጠሩ ግጭቶችን እና አዳዲስ አጀንዳ ፈጠራዎችን ያካትታል፡፡፡ 5. የአማራ ህዝብ የህለዉናዉ ስጋቶች 5.1. ከዉስጥ 5.1.1. መዋቅራዊ እና ስልታዊ ሁኖ ኢትዮጵያን ለማፍረስ እና አማራን ለማፅፋት በ 1987 ዓ.ም ስራ ላይ የዋለው የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት 5.1.2. ከራያ ከወልቃይት ከመተከል ከከሚሴ ከደራ ከአዲስ አበባ ጋር በተገናኘ በኦሮሞ በትግሬ እና በባለሁለት-ማንነት ፖለቲከኞች እና ሙህራን የሚሰራ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ አሻጥር 5.1.3. አማራ በብዛት የሚገኝባቸው የ ደቡብ እና የደቡብ ምዕራብ የኢትዮጵያ ክፍል ለአማራው ከፍተኛ የህልዉና ስጋት መሆናቸው 5.1.4. አማራን እና አገውን ወክለናል በማለት በክልል እና በፌደራል የስልጣን መዋቅር ውስጥ ያሉ ሂሊና ሞራል ምግባር እና ብልጠት አልቦ ካቢኔዎች 5.1.5. የአምሓራ ክልል ህዝብን አንድነት ለመሸርሸር የሚሰሩ የህዋሓት ዘመን ተጠቃሚ ፖለቲከኞች የብልፅግና ዘመን ተጠቃሚ ፖለቲከኞች አኩራፊ ፖለቲከኞች የአዉራጃዊነት ሀሳብ አቀንቃኞች በጎጥ እና በሀይማኖት ሽፋን የግል ጥቅም አሳዳጆች እና ፀረ-አማራዎች የአማራ አንድነትን ለማላላት የሚሰሩት ሴራ 5.1.6. ወንድማማች እና የኢትዮጵያ ጥንት ህዝቦች በሆኑት አማራ እና አገው መካከል ቅራኔ ለመፍጠር የሚፈልጉ ጥቅመኞች 5.1.7. በሱዳን በግብፅ በሕዋሓት እና በኦነግ የሚደገፈው የቅማነት እና የከሚሴ ፖለቲካ 5.1.8. የጠላት አጀንዳ ያስፈፅሙ ዘንድ ከአረብ ሀገራት ከግብፅ ከአዉረፓ አገራት እና ከአሜሪካ ደጎም ያለ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግላቸዉ ባንዳዎች እና የሁከት እስትራቴጂስቶች 5.1.9. ፀረ- አማራ የአገር ዉስጥ ሚዲያዎች 5.2.1. ኢትዮጵያን ማፍረስ የሚፈልጉ ሀይሎች 5.2.2. የሊበራሊስት የኮንሰረቫቲቭ-ዲሞክራቲስት እና የሶሻሊስት አገራቶች የፖለቲካ የኢኮኖሚ እና የሀይማኖት ፍላጎት 5.2.3. የምስራቅ አፍሪካ ጅኦ-ፖለቲክስ 5.2.4. የጎረቤት አገራት ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ያለመረጋጋት ሁኔታ 5.2.5. ግብፅ የምትፈጥረው የውሃ ፖለቲካ ተፅኖ 5.2.6. ፀረ-አማራ የዉጭ ሚዲያዎች 5.2.7. በፀረ- አማራ በፀረ- ኢትዮጵያ እና በባንዳዎች እየተሰራ ያለው የውጭ ዲፕሎማሲ 6. የመደራጀት አስፈላጊነት 6.1. ካልተደራጀን እኛ ታላለቆቹ ሙተን ልጆቻችን ለዘመናት እንደ ኩርዳኖች ወይም እንደ ጅብሲወች የሚሳደዱ የሚደበቁ ወይም የሚታረዱ ይሆናሉ፡፡ 6.2. አሁን ያለንበት የኢትዮጵየ የፖለቲካ ዘመን በባህል እና በአጓጉል እምነት የተጠመዶየኦሮሞፖለቲከኞች የጠለፉት ሲሆን ፖለቲካው ፍታዊ ማድረግ የሚቻለው በጠነከረ ክንድ ነው ለዚህ ደግሞ ትብብር ወሳኝ ነው፡፡ ልብ በሉ የቲራስማከስ ፍትህ የጠንካሮች ፍላጎትን ትመስላለች የሚለው አባባል ጊዜው አሁን ነው፡፡ 6.3. ስንደራጅ ታሪካዊ የፍትህ ተቋም አቋቁመን የአማራን ፍትህ ያጓደሉ ሁሉ በፍትህ ነፃነታቸው ይጓደላል 6.4. ስንደራጅ በሀሰት ትርከት ያበጡ የስልጣን ተሸሚዎቻችንን () በፖለቲካ ክንዳችን እናደቃቸዋለን፡፡ 6.5. የኦሮሞ ሙህራን ፖለቲከኞች እና ተስፋፊዎች የኦሮሞን ግዛት ማስፋፋት () ላይ ተጠምደዋል፡፡ ከተደራጅን ይህን በቀላሉ እንመክተዋለን፡፡ 6.6. ስንደራጅ ጠንካራ የሆነ ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ መገንባት እንችላለን ይህም የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ግንኙነታችንን () ከአፋር ከጋንቤላ ከቤንሻንጉል ከኩምዝ ከወላይታ ከሲዳማ ከሀረር ከኢትዮ-ሶማሌ ከኤርትራ ከእስራኤል እና ከአማሃራ ወዳጅ ሀገራት ጋር በማሳደግ የበለጠ የአማራን ደህንነት ማስጠበቅ ያስችለናል፡፡ 7. መቀረፍ ያለባቸው ጎጅ አማራን እየጎዱ ያሉ ባህሪያት 7.1. ግላዊ ባህሪ( አንዳንዶቻችን እኔ ካልተጎዳዉ የወንድሜ ጉዳት ጉዳቴ አይደለም የሚል ግላዊ ባህሪ() አዳብረናል፤ ምናልባች ይህ ሊዳብር የቻለው ለረጅም ጊዜ ኢትዮጵያዊነትን ከሚያስቀድም ማህበረሰብ ስለወጣን ሊሆን ይችላል፡፡ አሁን ግን ይህ ጊዜውን የዋጀ ስላልሆነ መወገድ አለበት፡፡ ምክንያቱም በአሁኑ አደገኛ በሆነዉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አሰላለፍ ስንጎዳም ስንድንም ስንሞትም ሁሉም ሂደት ወደ ጋርዮሽ ስነ-ልቦና ማደግ አለበት፤ ከዚህ ባለፈ ከግላዊነት ባህሪ በመላቀቅ አማራን ለማትረፍ አጋዥ ይሆናሉ ካልናቸው አካላት ጋር አብረን መስራት ይኖርብናል(ሳጥናኤልም ጋር ቢሆን)፡፡ ካልቻልን ግን እኔ ከሌለዉበት እና ከእኔ በላይ ላሳር አይነት ዋልታ እረገጥ ሀሳብ ወጥተን ቢያንስ ወንድማችን ለመፈንከት የመጣ የባህርዛፍ ሽመል እኛንም ጭምር ሳይፈነክት እንደማይሰበር አዉቀን ከግላዊነት ወደ ቡድናዊነት ከፍ እንበል፡፡ ወዳጀ! የመኖር ህልዉናችን ቀይ መስመር ላይ ቁሞ ተዉን እኛ ኢትዮጵያዊነትን ብናስቀድም ይሻለናል ካልን ደግሞ ኑረንም ኢትዮጵያን ላናተርፋት ከሞትንም በኋላ ኢትዮጵያን ላናገኛት የባተልን ከንቱ ባተሌ እንሆናለን፡፡ ምክንያቱም ኢትዮጵያዊ መሆን የምንችለዉ በአማራነታችን ተደራጅተን ከሀይቅ በላይ የጠለቁ ጠላቶቻችን በሀሳብ እና በሀይል ልዕልና በልጠን ህልዉናችን ስናረጋግግጥ ነዉ፡፡ 7.2. ጥራዝ ነጠቅ ሀይማኖቶኞች በአሁኑ ሰዓት አማራ ሁነው ግን ኦረቶዶክስ እና እስልምና እምነትን ለግል እና ለፖለቲካ ጥቅም የሚጠቀሙ ግለሰቦች የአማራን ስቃይ ያበዙታልና የአማራ አብዮት ሊያርቃቸው ወይም ሊያምቃቸው ይገባል ካለበለዚያ ሁነኛ የአማራ ሞት የሚፋጠረው ሀይማኖትን አስታኮ በሚመጣ የሴራ ፖለቲካ መሆኑ ይታወቅ፡፡ አንባቢ ሆይ ይህን ግን ልብ በል!!! በወያኔ በኦነግ እና በኦሮሞ ፖለቲከኞች ከ 1964 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ገደል የሚወረወሩት አማራዎች ክርስቲያንም ሙስሊምም ናቸዉ፡፡ ጠላት አማራ ነህ ብሎ እንጅ ክርስቲያን ነህ ወይስ ሙስሊም ነህ ብሎ አያጠቃህም፡፡ወደ አማራ ክልል ስንመጣ ደግሞ… በመሪዎቻችን ድክመት ምክንያት ኦነግ አጀንዳ ቀርጦ እና ብር በጅቶ አማራን በሀይማኖት ለመከፋፈል በአማራ ክልል ላይ ከሰልጠነ ቆየ፡፡ ያሳዝናል! ይህን ሁኔታ ግን በይበልጥ አንዳንድ ተማሩ የምንላቸው በጥቅም በዝቀተኝነት እና በፖለቲካ የታሰሩ ሰዎች አልተደረዱትም ሁኖም በሚገባቸው መንገድ ይረዱ ዘንድ ይህ ማታገያ ፅሁፍ አሳብ ይሰነዝራል፡፡ 7.3. አዉራጃዊነት ሙዚቀዎቻችን እዩ ተማርን የሚሉትን ሰዎች ጠጋ በሉና አዳምጧቸው ምሳሌዎቻችንን አስታዉሱ ቅኔዉ በምን እንደሚዘረፍ ልብ በሉ፤ ከእነዚህ ዉስጥ አዉራጃዊነት አለ፤ አዉራጃዊነት እንደማንነት ተቀይሮ አጉል መፎካከር እና መኮፈሰን በማምጣት አማራን በተናጠል የሚያስመታ ክፉ በሽታ በመሆኑ መወገድ አለበት፡፡ ወሎ ሸዋ ጎጃም አዲስ አበባ እና ጎንደር የአማራ እርስቶች እንጅ በራሳቸው ማንነት አይደሉም ስለዚህ ልንቀኝ የሚገባን አማራ ላይ እንጅ አዉራጀዎቻችን ላይ አይደለም፡፡ 7.4. በአንዳነድ የገጠር ቦታዎች ልዩነትን ያለማክበር ጎጅ ባህል፤ ጎጅ የሚባሉ ባህላዊ እሴቶችን አለመቅረፍ ለምሳሌ ሰውን ፋቂ ሸማኔ እና ቡዳ እያሉ ማሸማቀቅ የአማራ አንድነትን ስለሚጎዳ መወገድ ያለበት ባህል ነው፡፡ 7.5. የሙህሩ እና መንግስታዊ ፖለቲከኞች አድረባይነት እና ተለጣፊነት ስር የሰደደ መሆኑ፤ይህ የሙህራን ለዘብተኛ ዝምተኛ እና ዘገምተኛ አቋም እንዲሁም የፖለቲከኞች አድር ባይነት እስካልተወገደ ድረስ ብዙ ቀጣይ ትዉልዶች በባርነት ቀንበር ስር ይሆናሉ፡፡ 8. የሚመለከታቸው ባለጉዳዮች የአማራን ህልዉና ለማረጋገጥ ትኩረት ሊሰጧቸው የሚገቡ የሚገቡ ነጥቦች 8.1. የክልሉን ህገ-መንግስት ማሻሻል 8.2. የክልሉን ባንዲራ ማሻሻል 8.3. በአገው ማንነት ከተደራጁ ልዩ ወይም ብሄራዊ ዞኖች ዉጭ ያሉ የልዩ ዞን አደረጃጀቶችን ማፍረስ:: የአማራ እና የአገው ብሄሮችን በተመለከተ የተለያዩ ምሁራን የተለያዩ ግንዛቤዎች አሏቸው፤ አንዳንዶች አማራ ከሴም መደብ ነው ብለው ይከራከራሉ፤ ሌሎች ደግሞ አማራ ከሴማዊ-ኩሽ መደብ ሲሆን አገው ደግሞ ከኩሽ መደብ ነው ይላሉ፤ ሌሎች በአማራ እና በአገው መካከል ምንም ልዩነት የለም ካሉ በኋላ አገው የአማራ አባት ነው ይላሉ፤ ለዚህ አለማ ግን ፀሀፊው የአንቶኒ ስሚዝ እና የዎከር ኮንነር የብሔራዊ ትርጉም መሰረት በማድረግ አማራ እና አገው እንደ አንድ ህዝብ ሊቆጠሩ ይችላሉ ብሎ ያምናል ፤ እነዚህ ሁለቱ ተመሳሳይ የስነልቦና ትስስር ያላቸው፤ የኢትዮጵያ የስልጣኔ ባለቤቶች የሆኑ፤ ተመሳሳይ ታሪካዊ ትውስታ ያላቸው፤ ለረጅም ጊዜ የኦርቶዶከስ ሀይማኖት የሚከተሉ ለሶስትሽ ዓመታት የቆየ የፖለቲካ ባህል ያላቸው እና ተመሳሳይ ባህል ያላቸው በስሜን ኢትዮጵያ ተዋልደው ተጋብተው የሚኖሩ ሁለት ግን አንድ ናቸው፡፡ ስለሆነም ያለውን የቋንቋ ልዩነት መሰረት ያደረገ መከባበር ሊኖር ግድ ነውና ከዚህ ጋር በተገናኘ የአገው እና የአማራ ኢሊቶች ሀገር አፍራሽ እና ደም አፋሳሽ ከሆነ የጠላት አጀንዳ እራሳቸውን ማራቅ ይኖርባቸውል!! አገው ማለት አማራ ነው! አማራ ማለት አገው ነው!!! ከዚህ ጋር በተገናኘ የሚመለከታቸው አካላት በሁሉቱ መካከል ቁርሾ ለመፍጠር የሚፈልጉ ቡድኖችን እና ግለሰቦችን ቀድሞ የማምከን ስራ መስራት አለባቸው፡፡ 8.4. እስካሁን ድረስ ከአማራ ጋር አብሮ እና ተዛዝሎ የኢኮኖሚ ሽባ እንዲሆን የተፈረደበትን የዋግኽምራ አካባቢ ህዝብ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ 8.5. የአገዎችን ቋንቋ ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ በትምህርት ደረጃ ሁሉም የአማራ ትዉልድ እንዲማር ማድረግ፤ ይህም ቋንቋ አማራን ለመከላከል የአማራ የጦር ኮድ ሁኖ ያገለግላል:: የትኛውን የአገው የቋንቋ ዓይነት( ኽምጣኛ ወይስ አዊኚ) ነው አማረኛ ተናጋሪ ተሎ ሊረዳው እና ሊናገረው የሚችል የሚለውን ጥያቄ ግምት ውስጥ በማስግባት የሚመለከተው አካል በአጭር ጊዜ ጥናት አስጠንቶ ትውልዱን የሁለት ቋንቋ ተናጋሪ ባለቤት ለማድረግ ወደ ስራ መገባት አለበት፡፡ 8.6. የተጠናከረ የወታደር አደረጃጀት መፍጠር፤ ከዚህ ጋር በተገናኘ በቋሚነት የሚታወቁ እንደ ፋኖ እና እንደ አማራ ልዩ ሀይል ዓይነት አደረጃጀቶች በቂ አይደሉም ይልቁን የአማራ ህዝብ በክልሉ ዉስጥ ይሁን ከክልሉ ውጭ የሚመጣበትን ማናቸውም ጥቃት ለመመከት በሎጅሰቲክ ኢትዮጵያ ውስጥ እና ውጭ ባሉ ሀይሎች የሚደገፍ መሪው የማይታወቅ ብዙ አይነት የወታደር እዝ ያስፈልገዋል፡፡ 8.7. ሃይማኖት የሚኖረው አማኝ ካለ ብቻ ነው!!! የህዝብ ህልውና አደጋ ውስጥ በመውደቁ የኦርቶዶከስ እና የእስልምና ሀይማኖት ሰባኪዎች የአማራ ክልል ህዝብ ጠላትን አብሮ አንድ ሁኖ እንዲመክት መስበክ አለባችው፤ ይህን የሚመለከታቸው አካላት ማስፈፀም ይኖርባቸዋል፡፡ 8.8. ተራማጅ ያልሆኑ ሆዳቸውን ያስቀደሙ በማንነት ቀውስ ውስጥ ወድቀው ሌሎችን የሚጥሉ ህዝብ ወክያለው ብለው ህዝብን የሚሸጡ በሌብነት እና በግድያ እጃቸው የከሰረ ሁሉ የእጃቸውን ማግኘት ስላለባቸው ገዳይ ቡድን ያስፈልጋል፤ ይህ ገዳይ ቡድን በስራው ወቅት ስህተት እንዳይፈጠር የሚመለከተው አካል ሱፕረቫይስ ማድረግ አለበት፡፡ 8.9. የተጠናከረ የፋይናንስ ተቋም መገንባት እና ኢኮኖሚን ማሳለጥ 8.10. ከፍተኛ የክልል ስልጣን ቦታቸወን ሙሉ በሙሉ አማሃራ ማንነት ባላቸዉ እና በመጠላለፍ ፖለቲካ በተካኑ ፖለቲከኞች መሙላት 8.11. ከቀበሌ እስከ ክልል ያለዉን ካቢኔ አንስቶ ተራማጅ በሆነ አዲስ ካቢኔ መተካት 8.12. በክልሉ ከፍተኛ የስልጣን ቦታ ላይ ያሉ የቅማንት እና የከሚሴ-ኦሮሞች አመራርን ድምፅ አልባ ማድረግ 8.13. በአማሃራ ቴሌቪዥን ለሶማሌኛ ለኩናማኛ ለሲዳመኛ ለኩምዘኛ ለወላይተኛ ለኤርትራ-ትግረኛ እና ለአፋራኛ ቋንቋወች የአየር ሰዓት መስጠት 8.14. ከኢትዮ-ሶማሌ ከአፋር ከወላይታ ከሲዳማ ከቤንሻንጉል ኩምዝ ህዝቦች ጋር የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ትስስር ማድረግ 8.15. ኤርትራን የረጅም ጊዜ ወዳጅ ለማድረግ መስራት፤ እንዲሁም የስሜን ህዝብን በደል የተረዱ ህዋሓት በአማራ ህዝብ ላይ ያደረሰውን በደል የሚቀበሉ እና የወልቃይትን የይገባኛል ጥያቄ ፍፁም የማያነሱ ትግራዋይ ግለሰቦችን ይሁን ቡድኖችን ከትልቅ ጥንቃቄ ጋር ማቅረብ አስፈላጊ ነው፡፡ 8.16. የሰለጠነ የዉጊያ ስልት መንደፍ እና ከዎዳጅ አገራት ጋር የጦር ዲፕሎማሲን ማጠናከር፤ የሚመለከተው ሁሉ በተገኘው አጋጣሚ ፐሮቶኮሉን ያልጠበቀ ኢመደበኛ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ከውጭ ሀገራት ጋር ማድረግ ይኖርበታል!!! እያንዳንዱ ዲፕሎማት ዲፕሎማሲ የማታለል ጥበብ መሆኑን በመረዳት ጠላትም ወዳጅም ከሁኑ ሀገራት ፊት ፅጌረዳ ሁኖ መቅረብ አለበት፡፡ 9. አማራን ወደ ቀድሞው ማንነቱ ሊመልሱ የሚችሉ መልካም አጋጣሚዎች 9.1. ከፍተኛ የሆነ የሰዉ ካፒታል () እና የተፈጥሮ ሀብት() ያለዉ በዚሁ በአማራ ክልል መሆኑ 9.2. የተዳከመዉን የማዕከላዊ የፖለቲካ ስርዓት ስልታዊ እና እስትራቴጅካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም 9.3. አዲስ አበባ ላይ ጠንካራ የፖለቲካ ስርዓት መዘርጋት ኢኮኖሚዉን ደግሞ ወደ ባህርዳር መሳብ 9.4. የአማራ ህዝብ ዘላለማዊ ጠላት የነበረው ህዋሓት መዳከም 9.5. የኦሮሞ ፖለቲካ ለመረዳት የቀለለ መሆኑ 9.6. በኦሮሚያ ክልል ዙሪያ ያሉ ብሄሮች በኦሮሞ አክራሪዎች እየተጠቁ መምጣታቸው 9.6. ያለንን ጠንካራ እና የተደራጀ የታሪክ መሰረት በአግባቡ መጠቀም፤ ይህም የአማራን ታሪክ በአግባቡ መሰነድን እና የተሳሳቱ ታሪኮችን ማረም እና ትዉልድን ታሪክ ማስተማርን ያካትታል፡፡ 9.7. ከሳይበር ወደ መሬት የወረደ ትግል ማድረግ ዋቢ መፅሀፍት ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት፣ አምሓራ ህዝብ ላይ የደረሰ እልቂት፤ ጆርጂያ፣ 2015 እ.ኤ.አ አለቃ ታየ ገብረማሪያም፣ የኢትዮጵያ ታሪክ፣1898 አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣የአማረኛ መዝገበ ቃላት፣ አዲስ አበባ፣የኢትዮጵያ ቋንቋወችና ባህል አካዳሚ፣2006 አንቶኒ ስሚዝ፣ የብሄር ማንነት አተረጓጎም፣ 2001 እ.ኤ.አ ግርማ ሰይፉ፣ የተከበሩት፣ አዲስ አበባ፣2008 ይሁኔ አወቀ፣አምሓራነት፣ አዲስ አበባ፣2010 ዓስራት ዘዉዴ፣ ያለቃ ታየ ገብረማሪያም የኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ በአጭር ቀል የወጣ፣አዲስ አበባ፣ 2008 ሄነሪ ወቶን የሚባል የአስራ ሰባተኘዉ ክፍለ ዘመን የኢንግላንድ ዲፕሎማት ስለ አምባሳደር ምንነት ሲናገር አምባሳደር ማለት አንድን ሀገር ወክሎ ወደ ዉጭ ሀገር የሚላክ ታማኝ የሆነ ሰዉ እና የሀገሩን ጥቅም ለማስከበር ሲል በአንድ ጉዳይ መዋሸት ካለበት የሚዋሽ ሰዉ ነዉ ይላል። ለባለፉት 27 እና 3 ዓመታት ግን ኢትዮጵያን ወክለዉ የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስከበር እና ኢትዮጵያ ከሌላ ሀገር ጋር ያላትን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ትስስር ያጠናክራሉ የተባሉት አምባሰደሮች አብዛኞቹ ሕዋሓት እና ኦነግ የሚባል ማፊያ ቡድን ጋር በመወገን የሀገሪቱ ሀብት እና ቅርስ እንዲዘረፍ መንገዱን ያመቻቹ፤ ዉጭ ያሉ ኢትዮጵያኖች ሲገደሉ ሲዘረፉ እና ሲደፈሩ ምንም አልሆኑም ብለዉ የሚያስተባብሉ እንዲሁም የሀገሪቱን ጥቅም ለሌላ ወገን አሳልፈዉ የሚሰጡ ኮንትራቫዲስቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች በምንም ታምር አማራ ላይ የሚካሄደዉን ግድያ እንግለት እና የዘር-ማፅዳት ዘመቻ ለአለም ህዝብ ማስተዋወቅ አይፈልጉም፡፡ ሰዎች በባለፈዉ ዘመን በሆነ አካል ተበድለዉ ይሆናል፡፡ ያንንም የቆየ በደል በፍትህ መካስ ይፈልጋሉ፡፡ የሚመለከተዉም አካል ታሪክን ወደ ኋላ አይቶ ታሪካዊ ፍትህ ይሰጣል፡፡ ይህ አይነት ፍትህ ታሪካዊ ፍትህ () ይባላል፡፡ ታዲያ ታሪካዊ ፍትህ ለመስጠት የታሪካዊ ፍትህ ተቋም ያስፈልጋል ለምሳሌ አለም-አቀፍ የወታደር ፍርድ ቤት በ ኑርመብረግ () ከሁለተኛዉ የአለም ጦርነት በኋላ በሁለተኛዉ የአለም ጦርነት በዘር ማጥፋት እና በከባድ ኢ-ሰባዊ ድርጊት የተሰማሩ የጀርመን ወታደሮችን ወደ ፍርድ ለማቅረብ ተቋቋመ፡፡ ብዙ ወንጀሎኞችም በዚህ ተቋም ተጠየቁ ፍርድም ተሰጣቸዉ፡፡ ሌላዉ ከአፓርታይድ ስርሃት በኋላ በደቡብ አፍሪካ የተቋቋመዉ የደቡብ አፍሪካ የእዉነት እና የእርቅ ኮሚሽን ነዉ()፡፡ አማራም አማራ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀሙትን ለመቅጣት ታሪካዊ የፍትህ ተቋም ይኖረው ዘንድ ሁን ይደራጅ፡፡ አማሃራ ነህ? ከሆንክ መጥፎ ጊዜ ላይ ነዉ ያለኸዉ! ህልዉናህ አደጋ ላይ ነዉ ስለሆነም ከሳይበር እና ከሚዲያዉ ትግል አሁኑኑ ወደ መሬት ወርደህ ተደራጅ! ተደራጅተህ እራስህን ጠብቅ በጎበዝ አለቃ ተደራጅ የአካል አንቅስቃሴ ልመድ ከክላሽ ጋር ተወዳጅ፡፡ በሂወት ለመቆየት ያለህ ሌላኛው አማራጭ ከሳይበር ወደ መሬት የወረደ ትግል ማድረግ ነው፡፡
2413
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%89%A1%E1%89%A5%20%E1%89%A5%E1%88%94%E1%88%AE%E1%89%BD%20%E1%89%A5%E1%88%94%E1%88%A8%E1%88%B0%E1%89%A6%E1%89%BD%E1%8A%93%20%E1%88%95%E1%8B%9D%E1%89%A6%E1%89%BD%20%E1%8A%AD%E1%88%8D%E1%88%8D
ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል
የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች (የድሮ ክልሎች 7,8,9,10,11) በኢትዮጵያ ከሚገኙ አስራአንድ ክልሎች አንዱ ነው። 105,887.18 ካሬ ኪ.ሜ. ቦታ የሚሸፍን ሲሆን በምዕራብ በጋምቤላ፣ በደቡብ ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ ሰሜን ምሥራቅና ደቡብ ምሥራቅ በኦሮሚያ፣ በደቡብ ከኬንያ ጋር ይዋሰናል። የክልሉ ዋና ከተማ ሃዋሳ ሲሆን ሌሎች ትልቅ ከተማዎች ወልቂጤ፣ ጉብርየ፣ አርባ ምንጭ፣ ሆሳዕና፣ቡታጂራ፣ ክብረመንግሥት፣ ያቤሎ፣ አላባ፣ አገረሠላም፣ አለታዎንዶ፣ ቦዲቲ፣ ወንዶ፣ ዲላ፣ ይርጋለም፣ ጂንካ፣ ሶዶ፣ ቦንጋ፣ ሚዛን ተፈሪ ናቸው። ክልሉ በ፲፫ ዞኖችና ፰ ልዩ ወረዳዎች በ፳፪ የከተማ አስተዳደሮች የተደራጀ ሲሆን በ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. በተደረገው የሕዝብና ቤት ቆጠራ መሠረት 15,042,531 ሕዝብ የሚገኝበት ሲሆን ይህም ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 20.4% ይሸፍናል። ከዚህ በተጨማሪ በክልሉ ፶፮ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የሚኖሩ ሲሆን የእነዚህም ቋንቋዎች በአፍሮ እስያዊ (ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ ንዑስ ክፍሎችን ጨምሮ) እና ናይሎ ሳህራዊ የቋንቋ ቤተሰቦች ይመደባሉ። መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በኢትዮጵያ ካርታ ውስጥ ከ34° 88′ እስከ 39°14′ ምሥራቅ ኬንትሮስና ከ4°43′ እስከ 8° 58′ ሰሜን ኬክሮስ መካከል ይገኛል። ክልሉ 4207 ሜትር ከፍታ ካለው የጋሞ ጐፋው ጉጌ ተራራ እስከ 376 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ከፍታ ያለው የደቡብ ኦሞው ጨልባና ቱርካና ኃይቅ አካባቢ ያለው ዝቅተኛ ቦታን ጨምሮ በርካታ የተለያየ መልክዐ ምድራዊ አቀማመጥን ይዟል። በሐሩር፣ በቆላ፣ ወይናደጋና ደጋ የአየር ንብረትን የተከፋፈለ ሲሆን ለእርሻ ከብት እርባታ ምቹ የሆነና በደንም የተሸፈነ ክልል ነው። የአዋሣ የአባያ፣ ጫሞ፣ጨው ባህርና ቱርካና የመሳሰሉ ኃይቆች ኦሞ፣ጐጀብና ብላቴ ወንዞች ባለቤትና ከገናሌ-ዳዋ ከባሮ-አኮቦ፣ ከኦሞ-ግቤ፣ በአጠቃላይ 32% የሚደርሱ ተፋሰሶችንም ይጋራል። የአጆራ፣ሎጊታና ጋቺት ፏፏቴዎች የነጭ ሣር፣ኦሞ ማዜና የማጐና የጨበራ ጩጩራ ብሔራዊ ፓርኮች የሚገኙበት ነው። አስተዳደራዊ መዋቅር የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግሥት የተዋቀረው በሕግ አውጭው፣ ሕግ አስፈፃሚውና የዳኝነት (ሕግ ተርጓሚ) አካላት ነው። ከሌሎች ክልሎች በተለየ መልኩ የክልሉ ፖርላማ በሁለት ምክር ቤቶች ተዋቅሯል። እነዚህም የክልሉ ምክር ቤትና የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ናቸው። የህግ አስፈፃሚው የመስተዳድር ምክር ቤት በርዕሰ መስተዳድሩ የሚመራ ሲሆን የዳኝነት አካል በጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ይመራል። የሁሉም አካላት አወቃቀር ከብሔረሰቦች ም/ቤት በስተቀር በተዋረድ በክልሉ ውስጥ በሚገኙ ፲፫ ዞኖች፣ ፰ ልዩ ወረዳዎች በጠቅላላ የልዩ ወረዳዎችን ጨምሮ በ፻፴፬ ወረዳዎችና ፴፱፻፲፮ ቀበሌዎች ድረስ በተመሣሣይ ሁኔታ ተዋቅሯል። ተፈጥሯዊ ቦታዎችና ታሪካዊ ቅርሶች በጥናት ከተደረሰባቸው ታሪካዊ ቦታዎችና ቅርሶች ግንባር ቀደሙ በክልሉ በሁሉም ቦታ ተሠራጭቶ የሚገኝ ትክል ድንጋይ ሲሆን በአጠቃላይ ከ፲ሺህ በላይ እንደሆነ ይገመታል። ከእነዚህ ውስጥ አንድ ላይ ጥቅጥቅ ብለው በተለያዩ ሥነ ቅርጽና መልክ የተደረደሩትና የተተከሉት በጉራጌ ዞን የሚገኘው ጢያ በ1980 እ.ኤ.አ. በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት ተመዝግቧል። በክልሉ በርካታ ዋሻዎች ሲገኙ ከእነዚህ ውስጥ ሞቼ ቦራጐና አክርሳ ዋሻ /ወላይታ/ እና በጌዴኦ የሚገኙ የተቦረቦሩ ፭ የሥነ ድንጋይ ዋሻዎችና ቱቱ ፈላ ትክል ድንጋይ ግንባር ቀደሞቹ ናቸው። በሌላ በኩል በክልሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ የታወቁ የፓሊዮ አንትሮፖሎጂ አርኪዮሎዲጂ ቦታዎች ይገኛሉ። ከእነዚህ ውስጥ የታችኛው ኦሞ ሸለቆ አካባቢ /ሸንጋራ፣ ኡስኖ፣ ኪብሽና ሙርሲ አወቃቀሮ ች () የታወቀ ነው። የታችኛው ኦሞ ሸለቆ በ1980 እ.ኤ.አ. በዓለም አቀፍ ቅርስነት የዩኔስኮ መዝገብ ዝርዝር ገብቷል። ኮንሶ አካባቢ፤ ፋጀጅና ወይጦ አጭቀሬ በደቡብ ኦሞ ቡርጂ ቁሊቾ በቡርጂ ሌሎቹ የፓሊዮ አንትሮፖሎጂ ቦታዎች ይገኛሉ። በደቡብ ከሚገኙ ብሔሮች ስም እና ቋንቋዎች ዝርዝር ይህ ዝርዝር የተሟላ አይደለም ሶዶ ጉራጌ ሰባት ቤት ጉራጌ ቸሀ ጉራጌ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ዋነኛ የኢኮኖሚ መሠረት ግብርና ነው። ዋና ዋና ምርቶችም በቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍ፣ ጥራጥሬ፣ ድንች፣ እንሰት፣ ፍራፍሬዎችና የቅባት ሰብሎች ናቸው። ዋነኛው ምርት በእህል ራስን ለመቻል የሚያስችሉ ሲሆኑ ጐን ለጐን ገበያ ተኮር የሆኑ ቡና፣ ሻይ ቅጠል፣ ጐማ ተክል ወዘተ እንዲሁም ማንጐ፣ አኘል፣ አቦካዶ፣ አናናስ፣ ፓፓያና ሙዝ በስፋት ይመረታል። የቁም ከብቶች ወተትና የወተት ተዋፅኦም ይገኛል። ከግብርና በተጨማሪም በንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ በግንባታ፣ እንጨትና ብረታ ብረት፣ ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት የተደራጁ ማኀበራት ይገኛሉ። ማኅበራዊ ጉዳዮች በ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. የክልሉ አጠቃላይ ንፁህ የመጠጥ ውኃ ሽፋን 58% ደርሷል። ከዚህ ውስጥ የገጠሩ ሽፋን 57% ሲሆን በከተማ 66% እንዲሁም የተጠቃሚው ሕዝብ ብዛት 8.7 ሚሊዮን ድረስ እንደደረሰ መረጃዎች ያመለክታሉ። በክልሉ ያሉ ትምህርት ተቋማት ብዛት (ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል) 3,625፣ (ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል) 144፣ የመሰናዶ (ከ9-12) 44 ነው። በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረጃም 64 የመንግሥትና የግል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎች፣ ኮሌጆች /16ቱ አዋሣ ከተማ ውስጥ የሚገኙ/ እንዲሁም 5 ዩኒቨርሲቲዎች ይገኛሉ። አጠቃላይ የትምህርት ተሣትፎ በ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. መረጃ መሠረት 97.9% የደረሰ ሲሆን የሴቶች ተሣትፎ ወደ 84% አድጓል። የተማሪ መምህር ጥምርታ (1-4 ክፍል) 1፡66፣ 1፡42 ነው። የ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. የጤና ቢሮ መረጃ መሠረት በክልሉ 2,287 ጤና ኬላዎች 161 ጤና ጣቢያዎችና 16 ሆስፒታሎች ይገኛሉ። በአጠቃላይ የጤና ተሣትፎ ሽፋን 75% ደርሷል። መገናኛን በተመለከተ 2 ፖስታ ቤቶች፣ 2 ዋና ቅርንጫፍ ፖስታ ቤቶችና 44 ወኪል ፖስታ ቤቶች ሲገኙ ከ133 ከተሞች በላይ የዲጂታል አውቶማቲክና የሳተላይት ስልኮችን ይጠቀማሉ። በ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. መረጃ መሠረት በክልሉ የሚገኙ 130 የሚደርሱ ከተሞች የኤሌክትሪክ መብራት ያገኛሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ የ24 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን እጅግ በጣም ጥቂቶቹ በዲዚል ሞተር የሚንቀሣቀሱ የ12 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው፡፡ ሬድዮ፣ ቴሌቭዥንና ጋዜጣን በተመለከተ ሁለት የአካባቢ ሬድዮ ጣቢያዎች /«ፉራ ትምህርት ማሠራጫ ጣቢያ» እና «ወላይታ ሶዶ»/ እና በቅርቡ የተቋቋመው የደቡብ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ አዋሣ ይገኙበታል። ጋዜጦችን በሚመለከት «የደቡብ ንጋት» የተባለው የደቡብ ክልላዊ መንግሥት ጋዜጣ፣ በአዋሣ ከተማ ሽግግር አስተዳደር በአማርኛ የሚታተም «ዜና አዋሣ»፣ «ሚረር 3» የተባለ የግል ጋዜጣና በአርባ ምንጭ ከተማ የሚታተም «ትፍላሜ» የተባለውና በክልሉ ባህልና ማስታወቂያ የሚታተም «ማህደረ ደቡብ» የተባሉ ጋዜጦችና መጽሔቶች የሚታተሙ ሲሆን በየመ/ቤቱ የሚወጡ በርካታ ዓመታዊ መጽሔቶችም ይገኙበታል። በክልሉ መንግሥት እየተዘጋጀ በየቀኑ ከሰኞ እስከ እሁድ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ የሚተላለፍ የአንድ ሰዓት የቴሌቢዥን ኘሮግራም ይገኛል። የኢትዮጵያ ክልሎች
50349
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%8B%90%E1%88%9B%E1%8A%91%E1%8A%A4%E1%88%8D
ቅዱስ ዐማኑኤል
ይህ ኢየሱስ በዕብራይስጥ: ሲጻፍ፣ ፣ ሲነበብ፡ የሹዓ፣ ትርጉሙም፡ የሚያድን ማለት ነው፤ የክርስትና ሃይማኖት መሰረት ነው። ክርስቶስ በግሪክ ቋንቋ ሲጻፍ ፣ ሲሆን ፣ ይህም መሢሕ ማለት ነው :: በተጨማሪም ዐማኑኤል ይባላል ፣ (ኢሳያስ ም.፯ ቁ.፲፬ ) ፤ በዕብራይስጥ ሲጻፍ ፣ ፤ በግሪክ ሲጻፍ ፣ ሲሆን፣ ትርጉሙም እግዚአብሔር ከኛ ጋር ሆነ ማለት ነው። እየሱሰ በክርስትና ሃይማኖት አንድ አምላክ ከሚሆኑት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንዱ ወልድ እሱ ነው ፤ ይህም ወልድ ፣ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ እንደ ሰው በምድር ተመላልሶ የአባቱን መንግሥት አስተምሮ ለሰው ልጅ መዳን ሲል ራሱን አሳልፎ የሰጠ በመጨረሻም ከሞት ተነስቶ መንፈስ ቅዱስ እንዲተካው አድርጎ ወደ ሰማይ አርጎ በአባቱ ቀኝ የተቀመጠ ይህን ዓለም ለመፍረድ ዳግም ምፃቱ የሚጠበቅ አምላክ እና ፈጣሪ ነው ። ስለኢየሱስ የበለጠ ለመረዳት አዲስ ኪዳንን በተለይ ወንጌልን በአራቱ ሐዋርያት ፣ በቅዱስ ማርቆስ ፣ቅዱስ ሉቃስ ፣ ቅዱስ ዮሐንስ ፣ ቅዱስ ማቴዎስ የተፃፈውን ያንብቡ ። እንዲሁም አንዳንድ ሃይማኖቶች ደግሞ የእግዚአብሔር መልዕክተኛ ነው ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ነቢይ ነው ብለው ያምናሉ። ስምና ልደትበተጨማሪ «ኢየሱስ» የሚለው ስም ፦ በግሪክኛ «ኤሱስ» በቀዳማይ እብራይስጥ «ያህሹአ» ַ ፣ በደሃራይ እብራይስጥ «ያሱአ» ַ ፣ በአረማይክ «ዔሳዩ» ፤ በቀዳማይ አረብኛ «ዒሳ» ፤ በደሃራይ አረቢኛ «የሱዐ» ሲሆን ትርጉሙ ከእብራይስጥ «ያህዌ መድሃኒት ነው» ማለት መድኃኒያለም የሚል ፍቺ አለው፤ በተለይ ኢየሱስ ሰዎች ሲጠሩበት የነበረ የሰው ስም መሆኑን ለማሳየት ለሌሎች ሰዎች አገልግሎት ላይ ውሏል። የማርያም ልጅ ኢየሱስ ከሌሎች ኢየሱሶች ለመለየት ባደገበት አገር ስም በናዝሬት የናዝሬቱ ኢየሱስ ይባላል፦ ሉቃስ 18፥37። ከዚህም በቀር «ኢያሱ» (ወይም በግዕዝ «ኢየሱስ»፣ በግሪክ «ኢዬሶውስ»፣ በዕብራይስጥም «ያህሹዓ») የተባሉት ሌሎች ግለሠቦች ከብሉይ ኪዳን እና ከአዲስ ኪዳን ማየት ይቻላል፦ 1. የነዌ ልጅ ኢየሱስ - በሙሴ ዘመን ይኖር የነበረ ፍጡር ሰው ነው። 2. የኢዮሴዴቅ ልጅ ኢየሱስ - በሐጌ ዘመን ይኖር የነበረ ፍጡር ሰው ነው። 3. ኢዮስጦስ ኢየሱስ - የጳውሎስ ባልደረባ ነው (ቆላ.4:10-11)። እንደ ክርስትና እምነትና ወንጌሎች ኢየሱስ ከድንግል ማርያም እና ከመንፈስ ቅዱስ በቤተ ልሔም፣ ይሁዳ ተወለደ። ሳዱላዋ ማርያምና እጮኛዋ ዮሴፍ ለሕዝብ ቁጠራ በይሁዳ ስለ ተገኙ የቤት መጻተኞች ሆነው በጋጣ ተኝተው ነበር፤ ኢየሱስም በግርግም የተኛ እንጂ አልጋ አልነበረም። ገሊላ ግን በስሜን እስራኤል ወይም ሰማርያ ቤተሠቡ የተገኙበት ኢየሱስም የታደገበት ሀገር ነበረ። የኢየሱስ ጥቅሶችና ትምህርቶች ቤተክርስቲያን ቅዱስ ብላ የምትጠቀምባቸው ፬ መጻሕፍት ወንጌሎች በማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስ እንደተጻፉት የኢየሱስን ትምህርትና ከሞላ ጐደል የሕይወት ታሪኩን ይገልጻሉ። በነዚህ ወንጌሎች መሠረት ኢየሱስ ሲያስተምር ብዙ ጥቅሶች ይገኛሉ። ለምሳሌ፦ «የአሕዛብ አለቆች እንዲገዙአቸው፡ ታላላቆቹም በላያቸው እንዲሠለጥኑ ታውቃላችሁ። በእናንተስ እንዲህ አይደለም...» (ማቴ 20፡25) በዚሁ ጥቅስ ኢየሱስ ዓለሙን እንደ ገለበጠ ተብሏል። በዚያን ጊዜ ይሁዳ በባዕድ አረመኔ ሕዝብ ከባድ ገዥነት ሥር ነበረችና፣ የአይሁዶች ሊቃውንት ከትንቢት የተነሣ ከሮሜ ዕጅ የሚያድናቸውን መሢሕ ይጠብቁ ነበር። ይህ አይነት ትንቢት ቢገኝም ኢየሱስ ያንጊዜ በጦርነት ስላላነሣ የአይሁድ መሪዎች ሊቀበሉት ፈቃደኛ አልነበሩም። ደግሞ «እግዚአብሔር ምኑን ይፈልጋል?» ለሚለው ለዘመናት ፍልስፍና ጥያቄ በመመልስ ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ትንቢተ ኢሳይያስ ውስጥ ይህን መልስ አገኝቶ ብዙ ጊዜ ያጠቁመው ነበር፦ «ምሕረት እፈልጋለሁ እንጂ መሥዋዕት አይደለም።» ለሚሰሙት ተከታዮቹ ግን አዲስ ጥያቄ ጠየቃቸው፣ እንዲህ ሲል፦ «ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?» (ማርቆስ 8:36) በወንጌላት በኩል እጅግ በርካታ ተመሳሳይ ትምህርቶች በቀላሉ ሊነቡ ይቻላል። ደግሞ ይዩ፦ አባታችን ሆይ ያስተማረው የክርስትና ጸሎት ወርቃማው ሕግ የሕገ ወንጌል መሠረት ኢየሱስ ማን ነውባጭሩ በተዋሕዶ አብያተ ክርስትያናት እምነት ትምህርት፣ የኢየሱስ ሰብአዊና መለኰታዊ ባሕርይ አንድ (ተዋሕዶ) ነው። ከካልኬዶን ጉባኤ ጀምሮ ግን በሮማ ቤተክርስትያን ትምህርት ዘንድ በሁለት ልዩ ልዩ ሰብአዊና መለኰታዊ ባሕርዮች ተለይቷል። ኢየሱስ ወልድ ሆኖ ከሥላሴ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ) አንዱ ክፍል በመሆኑ አምላክ ነው በማለት በንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት ይስማማሉ። «ቃሉ ሥጋ ሆነ» ሲባል፣ ፈጣሪው ወደ ፍጥረቱ በሙሉ በመግባት ዓለሙን ለማዳን ኃይልና ፈቃድ እንዳለው ገለጸ ለማለት ነው። ከዚህ በላይ ስለ ኢየሱስ ማንነት ብዙዎች አብያተ ክርስትያናት ከአዲስ ኪዳን ጠቅሰው እንደሚያስተምሩት የሚከተለውን እንረዳለን 1. ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ከሁለት ሺህ ዓመት በፊት በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ አንድ እንግዳ ሰው ብቅ አለ፡፡ ይህ ሰው በአለም ውስጥ የተወለደ ቢሆንም፣ ልክ እንደማንኛውም ሰው ሰብአዊ ማንነት ቢኖረውም ተራ ሰው አልነበረም። ከድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ተፀንሶ ወደ ምድር የመጣው፣ በሰው አምሳል የተገለጠው ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ ይህ ሰው (የእግዚአብሔር ልጅ) ነው (ሉቃስ 1፡26-35)፣ (ዮሐንስ 1፡1 እና ዮሐንስ 1፡14)። በብሉይ ኪዳን ስለሚመጣው መሢህ (ክርስቶስ) ሲተነበይ ከመጠሪያዎቹ አንዱ አማኑኤል በዕብራይስጥ «ኢሜኑ» (ከኛ ጋር) «ኤል» (አምላክ) ወይም አምላክ ከኛ ጋራ ማለት ነው። ምድር የእግዚአብሔር መረገጫ እንደ ተባለች (ኢሳይያስ 66:1 እና ማቴ. 5:35) ወደፊት «ከወንዝ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ» ለዘላለም የሚነግስ ብለው የተነበዩለት አምላክ የሚሉት እግዚአብሔር ነው። 2. ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣው ለተለየ ተልእኮ ነው የሰው ልጅ ከጠፋበት መንገድ ሊመልስ (ሉቃስ 19፡10)። ከጨለማ ስልጣን ሊያድነን (ቆላሲያስ 1፡13)፡፡ ነፍሱን ለእኛ ቤዛ አድርጎ ሊሰጥ፤ ደሙን ከፍሎ ሊገዛን (ማቴ 20፡28)፡፡ * በሕይወታችን ያለውን የሰይጣንን ሥራ ሊያፈርስ (1ዮሐ 3፡8)፡፡ የዘላለም ሕይወት ሊሰጠን (1ዮሐ 5፡11፣12)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 3፡16፣17 እና ዮሐንስ 10፡10 ይመልከቱ፡፡ አዲስ ልደት በመስጠት የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሊያደርገን (ዮሐ 1፡12)፡፡ በተጨማሪ 1ዮሐ 3፡1.2 ይመልከቱ ከአብ ጋር የነበረንን ሕብረት ለማደስ (1ዮሐ 1፡3)። 3. ኢየሱስ እግዚአብሔር ምን እንደሚመስል ሊያሳየን መጣ (ዮሐ 14፡7-11)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 1፡18 ይመልከቱ። የእግዚአብሔርን ፍቅር አሳየን (1ዮሐ 4፡9፣10)፡፡ በተጨማሪ ሮሜ 5፡8 ይመልከቱ። የእግዚአብሔርን ኃይል አሳየን፣ የታመሙትን፣ ሽባዎችን እና አይነስውራንን ፈወሰ (ማቴ 4፡24)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 9፡1-7 ይመልከቱ። ርኩሳን መናፍስትን አስወጣ (ማር 1፡34)፡፡ በተጨማሪ ማርቆስ 5፡1-17 ይመልከቱ። ተአምራትን አደረገ (ማር 4፡37-41)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 6፡1-21 ይመልከቱ። ሙታንን አስነሳ (ዮሐ 11፡43፣44)፡፡ 4. ኢየሱስ መከራችንን ተቀበለ ኢየሱስ በምድር ሕይወቱ እኛ የምንቀበለውን የሕይወት ችግሮች በሞላ አይቷል፤ ስለዚህም ሊራራልን ይችላል። (ዕብ 4፡15)፡፡ በተጨማሪ ማቴዎስ 8፡17 ይመልከቱ። 5. ኢየሱስ ስለእኛ በመስቀል ላይ ሞተ ኃጢአተኛ ሰዎች በሀሰት ኢየሱስን እንደ ወንጀለኛ ከእንጨት በተሰራ መስቀል ላይ ቸነከሩት፡፡ ራሱን ከዚህ ማዳን ቢችልም፣ አላደረገውም፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር አለሙን የሚያድነው በእርሱ የመስቀል ላይ ሞት ነበርና፡፡ ስዚህ ኢየሱስ ስለ እኛ ሞተ! (ማር 15፡16-39 ያንብቡ) (1ጴጥ 2፡24)፡፡ በተጨማሪ ኢሳያስ 53፡5፣6 ያንብቡ፡፡ 6. ኢየሱስ ስለእኛ ከሙታን መካከል ተነሳ ከሦስት ቀን የመቃብር ቆይታ በኋላ እግዚአብሔር ልጁን ከሙታን መካከል አስነሳው! (ማቴዎስ 28 ያንብቡ)፡፡ ትንሳኤውም ጭምር ለእኛ ሲል ነበር፡፡ (ኤፌ 2፡4-6)፡፡ በተጨማሪ ሮሜ 6፡4 ያንብቡ፡፡ 7. ኢየሱስ ለእኛ የሰማይን ደጅ ከፈተልን በምድር ላይ የነበረውን ሥራ በፈፀመ ጊዜ ኢየሱስ ወደአባቱ ዘንድ ወደሰማይ አረገ፡፡ ይህም ጭምር ለእኛ ነበር፡፡ ምክንያቱም አሁንና ለዘላለሙ ከእርሱ ጋር አብረን ለመኖር ወደ እግዚአብሔር መገኛ የምንሄድበት መንገድ ከፍቶልናል፡፡ (ዕብ 10፡19-22)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 14፡1-3 ይመልከቱ። ለተጨማሪ መረጃ የሚከተለውን አድራሻ ይጎብኙ፡ ተጨማሪ ማጣቀሻዎች ስለ ኢየሱስ የበለጠ ለማወቅ ኢትዮጵያንኦርቶዶክስዶትኮም የተባለ ድረገጽን ይጎብኙ። መጽሓፍ ቅዱስ
12347
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%8B%AD%E1%8A%AD%E1%88%8D%20%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8C%84%E1%88%8E%20%E1%89%A1%E1%8A%93%E1%88%AE%E1%89%B2
ማይክል አንጄሎ ቡናሮቲ
ማይክል አንጄሎ ዲ ሎዶቪኮ ቡናሮቲ ሲሞኒ (6 ማርች 1475 - 18 ፌብሩዋሪ 1564) በተለምዶ ማይክል አንጄሎ እየተባለ ይጠራ የነበረው የእንደገና መወለድ ተብሎ በሚጠራው ዘመን ይኖር የነበረ ኢጣሊያዊ ሰዓሊ ፤ ቀራጭ፤ ህንጻ ሰሪ፤ ገጣሚ፤ እና መሀንዲስ ነበር። ምንም እንኳን ቅንድብን ወደ ላይ ከማስነሳቱ ባሻገር ይጠቀምባቸው የነበረው ስነ ስርአቶች እጅግ በጣም ከፍተኛ ደረጃ በመሆናቸው የእንደገና መወለድ ሰው የሚል ቅጽል ስም አሰጥቶት ነበር። እሱን በመሳሰሉ ታላላቅ ሰዓሊዎች ለምሳሌ ሊዮናርዶ ዳቪንቺ። ማይክል አንጄሎ በረጅም የእድሜ ዘመኑ በሰራቸው በማናቸውም የስራ ውጤቶቹ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነበሩ። ታሪካቸው በደንብ ከተመዘገበላቸው የ16ኛው ክፍለ ዘመን ሰአሊዎችም አንዱ አድርጎታል። እጅግ በጣም ከሚወደዱት ሁለት ስራዎቹ መሀከል ፒየታ = ሐዘን እና ዳዊት የሚባሉትን ሰርቶ የጨረሰው እድሜው ሠላሳ ከመሆኑ በፊት ነበር። ምንም እንኳን ለስዕል የነበረው አመለካከት በጣም ዝቅተኛ ቢሆንም ማይክል አንጄሎ ሁለት ድንቅ የተባሉ ስእሎችን በጄሶ ላይ በመስራት ለምዕራቡ አለም አበርክቷል። ዘፍጥረትን ሲስቲኒ በሚባለው ቤተ ክርስቲያን ጣራ ላይ እና የፍርድ ቀን የተባለውን ደግሞ በሲስቲኒ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከመንበሩ በስተጀርባ በኩል በሮማ ከተማ ውስጥ ይገኛሉ። ማይክል አንጄሎን ልዩ ከሚያደርገው አንዱ ነገር የመጀመሪያው የምእራብ አለም ሰዓሊ በህይወት ዘመኑ እያለ የህይወት ታሪኩ የተጻፈለትም በመሆኑ ነው። ሁለት የተለያዩ ጸሃፊዎች በህይወት እያለ ታሪኩን ጽፈውታል። አንደኛው ጂዮርጂዮ ቫሳሪ ሲሆን እርሱም ማይክል አንጄሎ እንደገና መወለድ ካፈራቻቸው የኪነ ጥበብ ሰዎች አናት ነው ብሎ ከፍተኛውን ስፍራ ይሰጠዋል። እስከ አሁን ድረስም ይህ አባባል እንደቀጠለ ይገኛል። በህይወት ዘመኑም እያለ የተቀደስው ወይም የተባረከው የሚል ቅጽል ስም አሰጥቶት ነበር ። የወጣትነት ጊዜው የሎሬንዞ ዲ ሜዲቺ ሞት በ 8 አፕሪል 1492 ለማይክል አንጄሎ ትልቅ ለውጥ አምጥቶለታል ማይክል አንጄሎ የሜዲቺን አጥር ግቢ ትቶ ወደ አባቱ ቤት ተጓዘ። በሚቀጥሉት ወራትም ከእንጨት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለት ከእንጨት ቀርጾ ለፍሎሬንቲን ቤተ ክርስቲያን ሳንቶ ስፒሪቶ በስጦታ አበረከተ። በአንጻሩም በቤተክርስቲያኑ ሆስፒታል በነበረው ውስጥ የሰውነትን ቅርጽ እና አሰራር በሞቱ ሰዎች አስከሬን በሆስፒታሉ ውስጥ ተለማምዷል። ከ 1493 እና 1494 ግዙፍ የሆነ ዕምነ በረድ ገዝቶ ሄርኩለስን ቀረጸ። ይህ ቅርጽ በሺያጭ ወደ ፈረንሳይ ሄዶ የደረሰበት ጠፋ 1700. በ 20 ጄንዋሪ 1494 በጣም ከፍተኛ በረዶ ከጣለ በኋላ ሎሬንዞ ፒኤሮ ዲ ሚዲቺ የበረዶ ቅርጽ ውድድር አዘጋጀ። ማይክል አንጄሎም ወደ ሜዲቺ ቅጥር ግቢ ለውድድር እንደገና ገባ። በዚያው አመት የሜዲቺ ቤተሰብ ከፍሎሬንስ ከስልጣን በሳቮናሮላ ተወገዱ። ማይክል አንጄሎ የፖለቲካው ግርግር ከማለቁ በፊት ፍሎሬንስን ትቶ ወደ ቬኒስ ከዚያም ወደ ቦሎኛ አቀና። በቦሎኛ አንድ ውል ተዋዋለ። ውሉም ተጀምሮ ያላለቀ የነበረ አንድ ትንሽ የዶሜኒኮ ሽራይንን ሀውልት ለመጨረስ ነበር። ይህም ቅርጽ የተሰራው ለዶሜኒኮ ማስታወሻ በሆነው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው። በ1494 መጨረሻ ግድም በፍሎሬንስ የፖለቲካው ሁኔታ ተረጋጋ ። ቀደም ሲል ከተማዋ በፈረንሳይ ትወረራለች የሚል ፍርሀት ነግሶ ነበር። ነገር ግን ቻርልስ ፰ኛው ሽንፈት ስለገጠመው ፍርሀቱ ተወግዶ ነበር። ማይክል አንጄሎ ወደ ፍሎሬንስ ተመለስ። ነገር ግን ከአዲሱ ሳናቫሮላ መንግስት ምንም አይነት ስራ አላገኘም። ከዚያም ወደ ሚዲቺ በመሄድ ስራ ከዚያ ጀመረ። . ፍሎሬንስ ባሳለፈው ግማሽ አመት ውስጥ ሁለት ትንንሽ ቅርጾችን ቀርጿል የመጀመሪያው መጥምቁ ዮሀንስ በልጅነቱ እና ሁለተኛው ደግሞ ኩፒድ የተኛው የፍቅር አምላክ የሚባሉ ነበሩ። ኮንዲቪ እንደሚለው ለሎሬንዞ ዲ ፒዬሬ ዲ ሜዲቺ ነበር መጥምቁ ዮሀንስን የቀረጸው። ነገር ግን ሌላኛውን «ተቀብሮ እንደተገኘ አሮጌ አስመስለው» ጥሩ ዋጋ እንዲያወጣልን በማለት ይነግረዋል። ከዚያም እንደተባለው ያደርግርጋል ። ከዚያም ቅርጹ እንደ አሮጌ ተደርጎ በሶስተኛ ሰው አማካኝነት ወደ ሮማ በመላክ ከዚያ ገዢ ተገኝቶ ይሸጣል። ሁለቱም ሎሬንዞ እና ማይክል አንጄሎ ክፉኛ ከተታለሉ በኋላ ራፋኤል ሪያሪዮ ቅርጹን ከሎሬንዞ የገዛው ሰው እንደተባለው አሮጌ እንዳልሆነ አወቀ። ነገር ግን በቅርጹ ጥራት እና ውበት በመማረኩ ቀራጩን ወደ ሮማ እንዲመጣ ጋበዘው። ይህ ያልታሰበና የተቃና እድል ቅርጹን ከወግ አጥባቂዎች ፍሎሬንታውያን ውጭ ገዢ እና ተቀባይ ማግኘቱ ማይክል አንጄሎን ጥሪውን ተቀብሎ ወደ ሮማ ለመሄድ አበቃው ። ማይክል አንጄሎ ሮማ በ25 ጁን 1496 ገባ እድሜውም 21 ነበር። በ 4 ጁላይ በዚያው አመት ከራፋኤል ሪያሪዮ ጋር በመዋዋል ስራ ጀመረ ። ስራውም ሮማውያን ባከስ የወይን አምላክ ብለው የሚጠሩት ነበር ። ነገር ግን ሀውልቱ ተሰርቶ ሲጠናቀቅ ካርዲናሉ ስላልወደዱት በወቅቱ የባንክ ሰራተኛ የነበረ ጃኮፖ የሚባል ሰው ለግቢው አታክልት ማጌጫ ገዛው ። በኖቬምበር 1497 የፈረንሳይ አምባሳደር ጋር አንድ ውል ተዋዋለ ይህም ውል እጅግ በጣም ውብ እና ድንቅ የሆነው ፒየታ (ሐዘን) የሚባለው ነበር ። ውሉ የተፈረመው በኦገስት ወር በሚቀጥለው አመት ነበር ። በወቅቱ የተሰጠውም አስተያየት በእውነቱ ይህ ተአምር ነው ምንም ቅርጽ ከሌለው እምነ በረድ ድንጋይ ይህን የመሰለ ቅርጽ መውጣቱ ፤ ተፈጥሮ እንኳን እንዲህ ያለውን መስራት አይቻላትም የሚል ነበር ። ማይክል አንጄሎ በሮም ውስጥ ሳንታ ማርያ ዲ ሎሬቶ አካባቢ ይኖር ነበር። እዚህም በሚኖርበት አካባቢ ቪቶሪያ ኮሎና ማርኩዚዬ ፔስካራ እና ገጣሚ ሴት ጋር ፍቅር ይዞት እንደነበር ይነገራል ። ይኖርበት የነበረው ቤት በ1874 ተደምስሷል ቀሪው አንዳንድ ተርፈው የነበሩ እና በአዲሱ ባለቤት ተቀምጠው የነበሩ እቃዎችም እንደገና በ1930 የመደምሰስ እጣ ገጥሟቸዋል። ዛሬ አዲስ የተሰራ የማይክል አንጄሎ ቤት የሚባል በጃኒኮሎ ኮረብታማ ቦታ ላይ ይገኛል ። በዚሁ ዘመን ነበር ማይክል አንጄሎ ላኩን እና ልጆቹ የሚባለውን ሀውልት ቀርጾ የጨረሰው ዛሬ ቅርጹ በቫቲካን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሮም ይገኛል የዳዊት ሐውልት ማይክል አንጄሎ ወደ ፍሎሬንስ ተመለሰ ከ1499–1501 ነገሮች በሪፐብሊክ አስተዳደሩ በኩል በጣም ተቀያይረዋል። በተለይም ጸረ እንደገና መወለድ ተቃዋሚ የነበረው ቄስ እና የፍሎሬንስ አስተዳዳሪ የነበረው ጂሮላሞ ሳቮናሮላ ( በ1498 ከተገደለ በኋላ ) እና የጎንፋላኖሪ ፒየር ሶዴሪኒ ከተነሳ በኋላ ። በወቅቱ አስተዳዳሪ የነበረው ጊልድ ዉል አንድ ጥያቄ ለማይክል አንጄሎ አቀረበለት ጥያቄውም አንድ ከአርባ አመት በፊት በአጎስቲኖ ዲ ዱቺዮ ተጀምሮ ያላለቀ ቅርጽ ነበር ። ቅርጹም እጅግ በጣም ግዙፍ የሆነ ለፍሮንቴናውያን የነጻነት ምልክት የነበረው ጎሊያድን በወንጭፍ መትቶ የገደለውን የዳዊት ሐውልት ነበር ። ቅርጹም ሊቀመጥ የነበረው ፒያዛ ዴላ ሲኞሪያ ሲሆን ይህ ቦታ የሚገኘው ከፓሎዞ ቪኪዮ ፊት ለፊት ነው ። ማይክል አንጄሎም የቀረበለትን ጥያቄ በሚገባ ሁኔታ ከተቀበለ በኋላ የዳዊትን ሀውልት ቅርጽ ከስራዎቹ ሁሉ በጣም ከሚወደዱት አንዱ የሆነውን ጨርሶ በ1504 አስረከበ ። ይህ አስደናቂ ቅርጽ ከአንድ ወጥ እምነበረድ ከካራራ ካብ ከወጣ እምነበረድ የተሰራ ሲሆን ቀደም ሲል በሌላ ሀውልት ቀራጭ ተጀምሮ ያልተጨረሰ ሲሆን ማይክል አንጄሎ ምን ያህል ከፍተኛ ችሎታ እና አስተሳሰብ እንዳለው ያስመሰከረበት ሐውልት ነው ። በዚሁ ዘመን ማይክል አንጄሎ የቅዱሳን ቤተሰብ እና ቅዱስ ዮሀንስ በሌላ ስሙ ዶኒ ቶንዶ ወይም ቅዱስ ቤተሰብ የሚባለውን ስእል ሰርቶ ጨርሷል ። ይህ ስእል የተሰራው ለአንጄሎ ዶኒ እና ማዳሌና ስቱሮዚ ጋብቻ ስጦታ ነው በ17ኛው ክፍለ ዘመንም ትሪቡን ኡፉዚ በሚባል ክፍል ውስጥ ተስቅሎ ይታይ ነበር ። ምናልባትም እመቤተ ማርያም እና ልጇንም ከመጥምቁ ዮሀንስ ጋር በሌላ ስሙ የማንቼስተር እመቤቴ ማርያም የሚባለውንም ስእል በዚሁ ዘመን ሰርቶ ጨርሷል ። ይህ ስእል በአሁኑ ጊዜ በለንደን ከተማ ብሄራው ጋሌሪ ሙዚየም ውስጥ ይገኛል። የሲስቲኒ ቤተ ክርስቲያን ጣራ በ1505 ማይክል አንጄሎ በአዲሱ ጳጳጽ ጁሊዬስ 2ኛው ጋባዥነት ወደ ሮም ተመለሰ ። ከዚያም አንድ ውል ተዋዋለ ውሉም ለጳጳጹ መቀበሪያ ለማሰናዳት ነበር ። ክፍያውም በቀጥታ ከፓፓጹ ነበር ። ማይክል አንጄሎ ይህን ስራ ብዙ ጊዜ እያቋረጠ ሌሎች ስራዎችን ያከናውን ነበር ። በዚህም የተነሳ ማይክል አንጄሎ በዚህ የመቃብር ስራ ላይ 40 አመት ፈጅቷል ። በመቃብሩ መካከል የሚገኘው የሙሴ ሀውልት ማይክል አንጄሎ እንደፈለገው አልተፈጸመም ። ዛሬ ይህ የሙሴ ሀውልት በቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን በቪንኮሊ ሮማ ቫቲካን ውስጥ ይገኛል ። በዚያው ዘመን ሌላ ውል ተዋዋለ ውሉም በሲስቲኒ ቤተክርስቲያን ጣራ ላይ ስእል ለመስራት ነበር ። ይህን ስእል ስርቶ ለመጨረስ አራት አመት ፈጅቶበታል (ከ1508 እስከ 1512 ) ማይክል አንጄሎ እንዳለው ብራማንቴ እና ራፋኤል ጳጳጹን አሳምነው ማይክል አንጄሎ ብዙ በማይወደው እና ብዙ ልምድ በሌለው የጄሶ ላይ ስእል ስራ ውል እንዲዋዋል አደረጉት ። ይህንንም ያደረጉት በወቅት በዚያን ዘመን ራፋኤል በጄሶ የስእል ስራ ከፍተኛ ከሚባለው ደረጃ ላይ ስለነበር በማይክል አንጄሎ ስቃይ እና ውድቀት ራሳቸውን ትልቅ አድርገው ለማሳየት ነበር ። ነገር ግን ይህን ታሪክ ዘመናዊ የታሪክ ተመራማሪዎች ይህን የሚያሳይ መረጃ ባለማግኘታቸው ታሪኩን አይቀበሉትም ። እንዲያውም ይህ የማይክል አንጄሎ አመለካከት ሊሆን ይችላል ይላሉ ። ማይክል አንጄሎ በመጀመሪያ የተዋዋለው የ12 ቱን ደቀ መዝሙሮች ስእል ለመስራት ነበር ። ነገር ግን ማይክል አንጄሎ በጣም የረቀቀ እና የተወሳሰበ ስእል እንዲሰራ አበክሮ ተከራከረ ለምሳሌ ዘፍጥረትን ያካተተ እንዲሁም የሰውን ልጅ ውድቀት እና በፈጣሪው የተገባለትን ቃል ኪዳን ከልጅ ልጅህ ተወልጄ ነጻ አውጣሀለሁ የሚለውን የኢየሱስ ታሪክ እና እንዲሁም ስለ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እምነት በስፊው እንዲያካትት ነበር ። ስእሉ በአጠቃላይ 300 ሰዎችን ያካተተ ሲሆን መሀሉም ዘጠኝ ክፍሎች አሉት ዘፍጥረትን ያካተቱ በሶስት ምድብ የተከፈሉ እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ሲፈጥር ፡ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሲፈጥር እና የግዚአብሐርን ቃል እንዴት መጠበቅ እንዳቃታቸው እና አህዛብን የሚወክለው ኖሕ እና ቤተስቡ ናቸው። የቤተክርስቲያኑን ጣራ መጋጠሚያዎች ላይ ደግሞ አስራ ሁለት ወንድ እና ሴት ነቢዮች የጌታችን የመዲሀኒታችን ኢየሱስ መምጣት ሲስብኩ ተስሏል ። ከእነዚህም ሰባት የእስራኤል ነቢያት ሲሆኑ አምስቱ ሴቶች ደግሞ ከሌላው አለም የተወከሉ ነበሩ ። በጣም ከሚወደዱት እና ከሚደነቁት እነዚህ ስእሎች መሀከል የአዳም አፈጣጠር እና ፡ አዳም እና ሔዋን በገነት የአትክልት ስፍራ ውስጥ የጥፋት ውሀ ፡ ነቢዮ ኢሳይያስ እና የሲቢል ነቢያት እና እንዲሁም የኢየሱስ ክርስቶስ ዘረ ሐረግ ናቸው ። ፍሎሬንስ በሚዲቺ ፓፓጽ ስር በ 1513 ጳጳጽ ጁሊየስ 2ኛው ሞቱ ። እሳቸውን የተካው ጳጳጽ ሌዮ ኤክስ ይባላል ። ማይክል አንጄሎ ክሜዲቺ ጋር አንድ ውል ተዋዋለ ውሉም በፍሎሬንስ የሚገኘውን የባሴሊካን ሳን ሎሬንዞ ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊቱን አፍርሶ የተለያዩ ቅርጾች እና ሐውልቶች ጨምሮ በተሻለ ሁኔታ ለመስራት ነበር ። ማይክል አንጄሎም በሀሳቡ ወዲያውኑ ተስማማ ። ከዚያም ለሶስት አመታት ለስራው የሚያስፈልገውን የስእል ንድፍ እና ለሐውልቶቹም የሚያስፈልገውን ንድፍ እና እቅድ አውጥቶ በአካባቢውም ለሐውልቶቹ ቅርጾች የሚያስፈልግውን የእምነ በረድ ካብ በፒዬትርራሳንታ ቁፋሮ ማካሄድ ካስጀመረ በኋላ በገንዘብ እጦት ምክንያት ስራው ተቋረጠ ። ማይክል አንጄሎ በህይወት ዘመኑ በጣም የተማረረበት የስራ ውል ነበር። ቤተ ክርስቲያኑም ምንም ለውጥ ሳይደረግለት እስከ ዛሬ ድረስ አለ ። ሜዲችም ቀደም ብለው በሰረዙት የስራ ውል ሳያፍሩ ማይክል አንጄሎን ሌላ ስራ እንዲሰራላቸው ጠየቁት ። በዚህ ጊዜ ደግሞ ለቤተሰባቸው የሚሆን የመቃብር ቤት በባሴሊካ ሳን ሎሬንዞ እንዲሰራላቸው። ይህ ስራ ከ 1520 እስከ 1530 ማይክል አንጄሎ ብዙ ጊዜ ሰርቶበታል ነገር ግን ስራው እስከ አሁን አልተፈጸመም ። ነገር ግን ማይክል አንጄሎ ምን ያህል ሐውልትን የመቅረጽ እና የምህንድስና ችሎታ እንዳለው የሚያሳይ ትልቅ ማስረጃ ነው ። ማይክል አንጄሎ ሐውልቶቹን እና የህንጻውን የውስጥ ፕላን በማውጣት ምን ያህል ከፍተኛ እና ድንቅ የሆነ ችሎታ እንዳለው አስመስክሯል ። እንደዘበት ብዙ ያስገረመው መቃብር የሁለቱ የማይታዩ ሜዲቺ በወጣትነታቸው የሞቱ የሎሬንዞ ማግኒፊኮ ልጅ እና የልጅ ልጅ እና እራሱ ሎሬንዞ ማግኒፊኮ የተቀበሩበት ያልተጨረሰ እና ብዙ የማያምር ባንድ ጎኑ በኩል ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር የሚዋሰን ነው ። በመጀመሪያ እንደታቀደው እመሬት ላይ የቆመ ቅርጽ የለውም ። በ 1527 የፍሎሬንስ ዜጎች በሮም አስተዳደር በመደገፍ ሜዲቺን ከስልጣን አስወግደው ሪፐብሊካን ስልጣን ላይ ወጡ። ከተማውን በመክበብ የትርምስ ጊዜ ሆነ ። ማይክል አንጄሎም የሚወዳትን ፍሎሬንስ በመርዳት ከ1528 እስከ 1529 በወታዳራዊ ተቋሞች ውስጥ በመስራት አገልግሏል ። በ 1530 የከተማዋ በሜዲቺ አስተዳደር ውስጥ ወደቀ ። ሜዲቺም ስልጣን ላይ ወጡ በሙሉ ስምምነት ከጨካኝ እና ጨቋኝ ከሆነው ዱካል ሜዲቺ ጋር ። ማይክል አንጄሎ ፍሎሬንስን በ 1530 ለቆ ወጣ ። የሜዲቺንም ቤተ ክርስቲያን እንዲጨርስ ስራውን ለሌላ ስው ስጥቶ ። ከአመታት በኋላም የማይክል አንጄሎ አስከሬን ከሮም ወደ ባሴሊካ ዲ ሳንታ ክሮሼ ለቀብር መቶ ነበር። ነገር ግን በማይክል አንጄሎ ኑዛዜ መሰረት እጅግ በጣም በሚወዳት ቱስካኒ የመጨረሻ ማረፊያው ሆነ የመጨረሻ ስራው በሮማ በጄሶ ላይ የፍርድ ቀን የተባለው የግርግዳ ላይ ስእሉ የተሰራው በሲስቲኒ ቤተ ክርስቲያን ከመንበሩ በስተ ጀርባ በኩል ነው። ይህ ውል የተፈጸመው ከጳጳጽ ክሌሜንቴ 8ኛው ጋር ነበር። ነገር ግን ጳጳጹ ውሉን በተዋዋሉ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። ፓውሎስ 3ኛው የዚህ ስራ ተቆጣጣሪ ነበሩ ማይክል አንጄሎም ስራውን ጀምሮ እስኪፈጽም ድረስ። ማይክል አንጄሎ በዚህ ስራ ላይ ከ 1534 እስከ 1541 ለሰባት አመት ሰርቷል። ስራው በጣም ግዙፍ እና ከመንበሩ በስተጀርባ ያለውን ገድግዳ ሙሉ በሙሉ ከጭፍ እስከ ጫፍ ያካተተ ነበር። የመጨረሻው የፍርድ ቀን የሚባለው ስእል የጌታችን የመድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛ ወደ ምድር ከጻድቃን ጋር ለፍርድ ቀን እንዴት እንደሚመጣ ለማሳየት የተሰራ ስእል ነው። ስእሉ ተስርቶ እንዳለቀ የብዙዎቹ ስእሎች ራቁታቸውን መሆን ጳጳጹ በሚጸልዩበት ቤተ ክርስቲያን በጣም ነውር እና አሳፋሪ ከምንሰራው ስራ ጋር የማይሄድ ነው በማለት ጳጳጽ ካራፋ እና ሞንሲኞር ሴሪኒኒ (የማንቱአ አምባሳደር) ስእሉ እንዲጠፋ ወይም ሀፍረተ ስጋቸው እንዲሸፈን ሲሉ በከፍተኛ ደረጃ ተቃወሙ። ነገር ግን በወቅቱ የነበሩት ፓፓጽ ስእሉ አይጠፋም ወይም አይቀየርም ሲሉ ክፉኛ ተከራከሩ። ማይክል አንጄሎ ከሞተ በኋላ ግን ሀፍረተ ስጋቸውን ለመሸፈን ተስማሙ። ከዚያም የማይክል አንጄሎ ተማሪ ከነበረው ዳኒኤሌ ዳ ቮልቴራ ጋር ውል በመዋዋል ሀፍረተ ስጋቸውን በጨርቅ መሸፈን ተያያዙት። በ 1993 ስእሎቹ እድሳት ሲደረግላችው ወግ አጥባቂዎች በጣም በመከራከር ቀደም ሲል ዳኒኤሌ ሸፍኗቸው የነበሩትን ስእሎች ቀድሞ ማይክል አንጄሎ እንደሰራቸው ማስመለስ ችለዋል። አንዳንዶቹንም ለታሪክ በማለት ጨርቅ እንደለበሱ ትተዋቸዋል። የማይክል አንጄሎ ስራዎች አሳፋሪ በሚል በሌላ ሰአሊ በመበላሸታቸው ዋናውን የማይክል አንጄሎ ዋና ስራ በማንም ያልተነካውን በማርቼሎ ቬኑስቲ የተሰራውን በካፖዲሞንቴ ሙዚየም ውስጥ ኔፕልስ ማየት ይቻላል። ሳንሱር ሁልጊዜ ማይክል አንጄሎን ይከታተለው ነበር ይባላል። ማይክል አንጄሎ በአንድ ወቅት የሚያሳፍር ስራ ፈጣሪ የሚል ስም ተሰጥቶት ነበር። ብዙ የማይወደደው የአሳማ ነገር በመባል የሚታወቀው የጸረ እንደገና መወለድ እንቅስቃሴ በዘመኑ የነበሩትን ቅርጽ እና ስእሎች በሙሉ ሀፍረተ ስጋ መሸፈን የተጀመረው በማይክል አንጄሎ ስራዎች ነው። ማስረጃ ለመስጠት ያህል የክርስቶስ ዴላ ሚንሬቫ ቤተክርስቲያን ሳንታ ማሪያ ሶፕራ ሚንሬቫ ሮም በጨርቅ እንዲሸፈኑ ተደርጓል እስከ ዛሬ ድረስ። ሌላው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሐውልት በልጅነቱ እራቁቱን የብሩጌስ ማዶና ። በቤልጂየም የሚገኘው የእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን ለብዙ ዘመን ሀውልቱ በጨርቅ ተሸፍኖ ይኖር ነበር። በለንደን በካስት ኮርትስ (ቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም ) ውስጥ የዳዊት ሀውልት ቅጂ ከበስተጀርባው ቅጠል በሳጥን ውስጥ ተደርጎ ይኖራል ምክንያቱም የንጉሱ ቤተሰቦች ሊያዩት ከመጡ እራቁቱን እንዳያዩት ለመሸፈን ተብሎ ነው። በ1546 ማይክል አንጄሎ የቅዱስ ፔጥሮስ ቤተክርስቲያን መሀንዲስ ሆኖ ተቀጠረ ። ከዚያም የቤተ ክርስቲያኑን አናት ግማሽ ክብ ንድፍ አውጥቶ ስራው ተጀመረ በዚያን ጊዜም ከፍተኛ ስጋት ነበር። ስጋቱም ስራው ከመጠናቀቁ በፊት ማይክል አንጄሎ ይሞታል የሚል ፍርሀት ነበር። ነገር ግን ግማሽ ስራው እንደተገባደደ ስራውን እንደሚፈጽሙት አረጋገጡ። የመጨረሻው ንድፍ መገኘት በዲሴምበር 7 2007 የማይክል አንጄሎ በቀይ ቾክ የተሰራ የቅዱስ ጴጥሮስ ባሴሊካ ንድፍ ተገኘ። በ 1564 ከመሞቱ በፊት። የተገኘውም በቫቲካን ግምጃ ቤት ውስጥ ነው። በጣም የሚያስገርም ነገር ነበር። ማይክል አንጄሎ ጥሩ ያልሆኑ የሚላቸውን ስራዎቹን በሙሉ በእሳት አቃጥሏቸዋል። የተገኘው ንድፍ ከቋሚዎቹ የአንዱ ሲሆን የቅዱስ ጴጥሮ ኩፖላ ድረም በመባል ይታወቃል። የሕንጻ ስራዎቹ ማይክል አንጄሎ በሌሎች ሰዎች ተጀምረው ባላለቁ በብዙ ስራዎች ላይ ተሳትፏል። በጉልህ ከሚታዩት ለምሳሌ የቅዱስ ጴጥሮስ ባሴሊካ እና ካምፒዶጊሊዮ ፕላናቸውን ያወጣው ማይክል አንጄሎ ነው። የሮማን ካፒቶል ሂልም ንድፍ ያወጣው ማይክል አንጄሎ ነበር። ቅርጹም ሮምቦይድ ነበር ከአራት ማእዘን ይልቅ ይህንንም ያደረገበት ምክንያት በቦታው ጥበት የተነሳ የተመልካቹን አይን ለማታለል ነው። ሌላው የህንጻ ስራዎቹ በፍሎሬንስ ሳን ሎሬንዞ እና የሎውሬንቲን ቤተ መጻህፍት እና ለውትድርና የሚያገለግሉ ምሽጎች እና ማማዎች ናቸው። በሮም ከሰራቸው ደግሞ የቅዱስ ጴትሮስ ቤተ ክርስቲያን ፤ ፓላዞ ፋርኔሴ ፤ ሳን ጆቫኒ ዴዪ ፊዮሬንቴኒ ፤ ዘ ስፎዛ ቤተክርስቲያን (ካፔላ ስፎርዛ) በ ባሴሊካ ዲ ሳንታ ማሪያ ማጆሬ ፤ ፖርታ ፒያ እና ሳንታ ማሪያ ዴጂሊ አንጄሊ ናቸው። የላውሬንቲን ቤተ መጻህፍት በ 1530 ማይክል አንጄሎ የላውሬንቲን መጽህፍት ቤት በፍሎሬንስ ንድፍ አወጣ። መጻህፍት ቤቱ ከሴንት ሎሬንዞ ቤተ ክርስቲያን ጋር የተያያዘ ነው። በዚህ ስራው ላይ ፒላስተርስ የሚባል አዲስ ዘዴዎችን በመጠቀም። ሌላው ከስር ከስተው ወደ ላይ እየወፈሩ የሚሄዱ ዘዴዎችን በመጠቀም ። ደረጃዎችን ደግሞ አራት ማእዘን እና ግማሽ ክብ አድርጎ በመፍጠር ነበር። የሜዲቺ ቤተ ክርስቲያን ማይክል አንጄሎ የሜዲቺን ቤተክርስቲያን ንድፍ አወጣ። በሜዲቺ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተለያዩ ሐውልቶች አሉ ለተለያዩ የሜዲቺ ቤተሰቦች የተሰሩ። ማይክል አንጄሎ ስራውን በሙሉ አልጨረሰውም። የሱ ሰራተኞች የነበሩ በኋላ ጨርሰውታል። ሎሬንዞ ዘ ማግንፊሰንት የተቀበረው ከመግቢያው ፊት ለፊት ነው። የእመቤቴ ማርያም እና ልጇ እንዲሁም የሜዲቺ አለቃ የሆኑት የቅዱስ ኮስማስ እና ዳሚያን ከመቃብሩ በላይ በሐውልት ተቀርጸዋል። የእመቤቴ ማርያም እና ልጇ ሐውልትም የተቀረጸው በማይክል አንጄሎ ነው። ማይክል አንጄሎ ብዙ ጊዜ እብሪት ለሌሎች ያሳይ ነበር እና በራሱም ብዙ አይደሰትም ነበር። ኪነ ጥበብ ከባህል እና ከውስጥ የሚመነጭ ስሜት እንደሆን ይናገር ነበር። በወቅቱ ተፎካካሪው ከነበረው ከሌዎናርዶ ዳቬንቺ በተቃራኒው። ማይክል አንጄሎ ተፈጥሮን እንደ ጠላት ነበር የሚያየው ስለዚህም መሸነፍ አለበት ይል ነበር። የሚሰራቸው ስራዎች በሙሉ እያንዳንዳቸው በየራሳቸው መንገድ አስደናቂ እና አስገራሚ ነበሩ በዘመኑ ከሚታዩት ሐውልቶች ። ማይክል አንጄሎ የሐውልት ቀራጭ ስራ የሚፈለገውን ቅርጽ ከ እምነበረዱ ውስጥ ማላቀቅ ነው ይል ነበር። ማይክል አንጄሎ እያንዳንዱ እምነበረድ በውስጡ ቅርጽ አለ ብሎ ይል ነበር የቀራጭም ስራ የማያስፈልገውን ቅርጹን የሸፈነውን እና የቅርጹ አካል ያልሆነውን እምነበረድ ከላዩ ላይ በመዶሻ እና በመሮ መቅረፍ ወይም ማለያየት ነው ይል ነበር። በወቅቱ ይነገር ከነበረው አፈ ታሪክ የማይክል አንጄሎ ችሎታ በተለይም ሐውልት በመቅረጽ ላይ በወቅቱ በጣም የተወደደ ነበር። ሎሬንዞ ደ ሚዲቺ በማይክል አንጄሎ ትንሽ ገንዘብ ሊሰራ ፈለገ። ማይክል አንጄሎንም የፍቅር አምላክ የሚባለውን ሐውልት እንዲሰራ እና አሮጌ እንዲያስመስለው ጠየቀው። ሎሬንዞ ለማይክል አንጄሎ ለፍቅር አምላክ ለሚባለው ቅርጽ 30 ዱካት ከፈለው። ነገር ግን ሎሬንዞ ቅርጹን አሮጌ ቅርጽ ለሚሸጡ ሰዎች በ 200 ዱካት ሸጠው። ቅርጹን የገዛው ካርዲናል ራፋኤል ሪያሪዮ ቅርጹ አሮጌ መሆኑን በጣም ስለተጠራጠረ የቅርጹን ታሪክ የሚያጠናለት ሰው ቀጠረ። ሰውየውም ማይክል አንጄሎን ካገኘው በኋላ የፍቅር አምላክ የሚባልውን ሐውልት በወረቀት ላይ ንድፉን እንዲሰራ እና እንዲያሳየው ጠየቀው ማይክል አንጄሎም ስርቶ አሳየው። በዚህን ጊዜ ሰውየው ከአንተ የፍቅር አምላክ የሚባለውን ቅርጽ በ 30 ዱካትስ ገዝቶ በ200 ዱካትስ እንደሸጠው ነገረው። ማይክል አንጄሎም ቅርጹን እሱ እንደቀረጸው ተናዘዘ ነገር ግን ይህን ያህል መታለሉን አላወቀም ነበር። እውነቱ ከወጣ በኋላ ካርዲናሉ ቅርጹን የገዛው ማይክል አንጄሎ በእርግጥም ልዩ ችሎታ እንዳለው ካረገገጠ በኋላ ባከስ ወይም የወይን አምላክ የሚባለውን እንዲሰራለት ውል ተዋዋሉ። ሌላው ሰለ ማይክል አንጄሎ የሚነገረው ታሪክ ሙሴ የሚባለውን ሐውልት ሰርቶ ሲጨርስ ይቀርጽበት በነበረው መዶሻ የሙሴን ሀውልት ጉልበቱን በመዶሻው በመምታት “ለምን አታናግረኝም” ብሎ እንደመታው ይነገራል። በግል ህይወቱ ማይክል አንጄሎ በጣም ቁጥብ ነበር ። ተማሪው ለነበረው"አስካኒዮ ኮንዲቪ “ምንም ሀብታም ብሆን የኖርኩት ግን እንደ አንድ ድሀ ነው ብሎት ነበር። ኮንዲቪ እንዳለው ለምግብ እና ለመጠጥ ብዙም ግድ አልነበረውም። የሚበላው ሲርበው ብቻ እንጂ በምግብ ለመደስት ብሎ በልቶ አያውቅም። ወደ አልጋውም ሲሄድ እስከ ልብሱ እና ጫማው ይተኛ ነበር። ይህ ጸባዩ በብዙዎች ዘንድ የተወደደ አልነበረም። ይህ ጸባዩ በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ እንዳይሆን አድርጎታል። ታሪኩን የጻፈው ፓኦሎ ጂኦቪዮ እንዳለው “ተፈጥሮው በጣም አስቸጋሪ እና ግልጽ ያልሆነ ነው። የቤት ውስጥ አያያዙም ባህሪውም ቆሻሻ ነበር። በዚህም የተነሳ ብዙ ተከታይ አልነበረውም ይላል። ማይክል አንጄሎ ግን ግድ አልነበረውም። በተፈጥሮው ከሰው ጋር ብዙ መገናኘት ስለማይወድ። ብዙዎችም ጉደኛው እና አስገራሚው ይሉት ነበር። ማይክል አንጄሎ እራሱን ከሰዎች አግልሎ ነበር ህይወቱን የኖረው። የማይክል አንጄሎ መሰረታዊ የኪነ ጥበብ ስራ መስረት ያደረገው የወንድን ጡንቻማ አካል በ መውደድ ላይ ነው። ወደዚህም የተሳበው ተፈጥሮን በጣም ስለሚወድ እና ስሜታዊ ስለነበር ነው። በከፊል የእንደገና መወለድ አገላለጽ እና አምልኮ ነበር። የማይክል አንጄሎም የስራ ውጤቶች ተፈጥሮን መውደዱን በግልጽ የሚያንጸባርቁ ነበሩ የሚቀርጻቸውም ቅርጾች ፍቅርን እና ተፈጥሮን የሚገልጹት በኒዮፕላቶኒያን እና በእርቃነ ስጋ ላይ ያተኮረ ነበር። ለምሳሌ ቺቺኖ ዴዪ ብራቺ በተዋወቁ በአመቱ በ 1543 ከዚህ አለም በመለየቱ አርባ ስምንት የሀዘን እንጉርጉሮ ግጥም ጽፎለታል። አንዳንድ ሰዎች ይህን በመመልከት ግንኙነታቸው ከጓደኝነት በላይ ነበር ይላሉ። ሌሎች ሰዎች ደግሞ የፕላቶኒያን ፍቅር መግለጫ መንገድ ነበር ይሉታል። በወቅቱ ሀፍረት የሌለበት ግጥም ለሚወዱት ሰው መግጠም እውነተኛ የፍቅር መግለጫ ነበር ይላሉ። በ 16 ኛው ክፍለ ዘመን የነበረው የሞያ ፍቅር ከዛሬው የሞያ ፍቅር በጣም የበለጠ ነበር። በወቅቱ የነበሩ አንዳንድ ወሮ በላዎችም ይህንን አጋጣሚ ገንዘብ ለማግኛ ተጠቅመውበታል። ፌቦ ዲ ፖጂዮ በ 1532 ማይክል አንጄሎ የጻፈለትን የፍቅር ደብዳቤ ይዞ ይዞር ነበር። ቀደም ሲል ጌራርዶ ፔሪኒ በ 1522 ያለ ሀፍረት ዘርፎታል። ማይክል አንጄሎ ራሱን ከሰው ያገል ነበር። አንድ የጓደኛው ሰራተኛ የነበረ ኒኮላ ኳራቴሲ የሚባል ሰው ልጁን ከማይክል አንጄሎ ጋር ተማሪ ሆኖ እንዲሰራ ሲጠይቀው አልጋም ላይ ጥሩ ነው ብሎት ነበር። ማይክል አንጄሎ ግን ወዲያውኑ ግብረ ሰዶም ለእሳት ይዳርጋል ብሎ መልስ ሰጥቶታል። ከፍተኛው የፍቅር ደብዳቤ ተጽፎ የተገኘው ለቶማሶ ዴዪ ካቫሌሪ ነው በወቅቱ እድሜው 23 አመት ሲሆነው ነው ከማይክል አንጄሎ ጋር የተገናኙት በ1532 ማይክል አንጄሎ 57 አመቱ ነበር ። ካቫሌሪ በእድሜ ከገፉ ሰዎች ጋር ይውል ነበር። ፍቅራችሁን እመልሳለሁ እያለም ይምል ነበር። እንዳንተ የወደድኩት ሰው የለም እያለም ይናገር ነበር። ጓደኝነትህንም ከማንም በላይ እፈልገዋለሁ እያለም ይናገር ነበር። ካቫሌሪም ማይክል አንጄሎ እስከሞተበት ጊዜ ድረስ ጓደኝነታቸው የጸና ነበር። ማይክል አንጄሎም ከሶስት መቶ በላይ ግጥሞች እና እንጉርጉሮ ጽፎለታል። አንዳንዶች እንደሚሉት ግን ይህ ፍጹም ንጹህ የሆነ ወንድማዊ የፕላቶኒያን ፍቅር መግለጫ ነው ይላሉ። እንዲያውም ማይክል አንጄሎ ካቫሌሪ ልጅ ቢኖረው ወስዶ ለማሳደግ ይፈልግ ነበር። ነገር ግን በወቅቱ ፍቅራቸው በግልጽ የሚታይ ነበር። ማይክል አንጄሎ ለግጥም እና ለቪቶሪያ ኮሎና ለምትባል ሴት ከፍተኛ ፍቅር ነበረው። የተገናኙት ሮም ውስጥ በ 1536 ወይም በ 1538 ነበር። ሲገናኙም ቪቶሪያ በ አርባዎቹ አመታት ውስጥ ነበረች። እስከሞተችበት ጊዜም ድረስ ግጥም ይጻጻፉ ነበር። ግንኙነታቸው ምን እንደነበር ለመገመት አስቸጋሪ ነበር። ኮንዲቪ ግን የመነኩሴ ንጹህ ፍቅር ነው ይል ነበር። ነገር ግን በግጥሞቹ እና በሰራቸው ስራዎቹ አስተሳሰቡን መገመት እንችላለን ይህን ይመልከቱ የማይክል አንጄሎ ስራዎች በከፊል የግርጌ ማስታወሻ በበለጠ ለማንበብ ወደ ውጭ የሚያገናኙ የጣልያን ሰዎች
52411
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A4%E1%88%8D%E1%8B%9B%E1%89%A4%E1%89%B5%20I
ኤልዛቤት I
ኤልዛቤት (ሴፕቴምበር 7 1533 - መጋቢት 24 ቀን 1603) [ሀ] የእንግሊዝ እና የአየርላንድ ንግስት ከህዳር 17 ቀን 1558 በ1603 እስከሞተችበት ጊዜ ድረስ የእንግሊዝ እና የአየርላንድ ንግስት ነበረች። አንዳንድ ጊዜ ድንግል ንግሥት እየተባለች የምትጠራው ኤልዛቤት ከአምስቱ የንጉሠ ነገሥታት ቤት የመጨረሻዋ ነበረች። ቱዶር. ኤልዛቤት የ21⁄2 አመት ልጅ እያለች የተገደለችው የሄንሪ ስምንተኛ እና ሁለተኛ ሚስቱ አን ቦሊን ልጅ ነበረች። የአን ከሄንሪ ጋር የነበራት ጋብቻ ፈርሷል፣ እና ኤልዛቤት ህጋዊ እንዳልሆነ ተነገረች። ግማሽ ወንድሟ ኤድዋርድ ስድስተኛ እ.ኤ.አ. በ 1553 እስኪሞት ድረስ ገዝቷል ፣ ዘውዱን ለሴት ጄን ግሬይ ውርስ በመስጠት እና የሁለቱን ግማሽ እህቶቹ የሮማ ካቶሊክ ማርያም እና የታናሽቷ ኤልዛቤትን የይገባኛል ጥያቄ ችላ በማለት ፣ ምንም እንኳን በተቃራኒው የሕግ ሕግ ቢኖርም ። የኤድዋርድ ኑዛዜ ወደ ጎን ቀረበ እና ማርያም ንግሥት ሆና ሌዲ ጄን ግሬይን ከስልጣን አወረደች። በማርያም የግዛት ዘመን ኤልዛቤት የፕሮቴስታንት አማፂያንን ትረዳለች ተብላ ተጠርጥራ ለአንድ ዓመት ያህል ታስራለች። እ.ኤ.አ. ንግሥት ሆና ካደረገችው የመጀመሪያ ተግባሯ አንዱ የእንግሊዝ የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን መመስረት ሲሆን ለዚህም ዋና አስተዳዳሪ ሆነች። ይህ የኤልዛቤት ሃይማኖታዊ ሰፈራ ወደ እንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን መቀየር ነበረበት። ኤልዛቤት አግብታ ወራሽ ታፈራለች ተብሎ ይጠበቅ ነበር; ይሁን እንጂ ብዙ መጠናናት ቢያደርግም እሷ ግን ፈጽሞ አላደረገችም። እሷ በመጨረሻ የመጀመሪያ የአጎቷ ልጅ ሁለት ጊዜ ተወግዷል, ጄምስ ስድስተኛ የስኮትላንድ; ይህም የታላቋ ብሪታንያ መንግሥት መሠረት ጥሏል። እሷ ቀደም ሲል የጄምስ እናት ማርያም፣ የስኮትላንድ ንግሥት ለእስር እና ግድያ ተጠያቂ ሆና ነበር። በመንግስት ውስጥ ኤልዛቤት ከአባቷ እና ከፊል ወንድሞቿ እና እህቶቿ የበለጠ ልከኛ ነበረች። አንዱ መፈክሯ "ቪዲዮ እና ታይኦ" ("አየሁ እና ዝም አልኩ") ነበር። በሃይማኖት በአንጻራዊ ሁኔታ ታጋሽ ነበረች እና ስልታዊ ስደትን አስወግዳለች። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በ1570 ዓ.ም ሕገ-ወጥ መሆኗን ካወጁ በኋላ ተገዢዎቿን ከመታዘዝ ከለቀቀች በኋላ፣ በርካታ ሴራዎች ሕይወቷን አደጋ ላይ ጥለውታል፣ ይህ ሁሉ በፍራንሲስ ዋልሲንግሃም በሚመራው የአገልጋዮቿ ሚስጥራዊ አገልግሎት ተሸነፈ። ኤልዛቤት በፈረንሳይ እና በስፔን ዋና ዋና ኃያላን መንግስታት መካከል በመቀያየር በውጭ ጉዳይ ላይ ጠንቃቃ ነበረች። በኔዘርላንድ፣ ፈረንሣይ እና አየርላንድ ውስጥ በርካታ ውጤታማ ያልሆኑ፣ በቂ ሀብት የሌላቸውን ወታደራዊ ዘመቻዎችን በግማሽ ልብ ብቻ ደግፋለች። በ1580ዎቹ አጋማሽ እንግሊዝ ከስፔን ጋር ጦርነትን ማስወገድ አልቻለችም። እያደገች ስትሄድ ኤልዛቤት በድንግልናዋ ተከበረች። በጊዜው በስዕሎች፣በገጸ-ባህሪያት እና በስነ-ጽሁፍ ይከበር የነበረው የስብዕና አምልኮ በዙሪያዋ ወጣ። የኤልዛቤት ንግስና የኤልዛቤት ዘመን በመባል ይታወቃል። ወቅቱ እንደ ዊልያም ሼክስፒር እና ክሪስቶፈር ማርሎው ባሉ ፀሀፊ ፀሃፊዎች የሚመራ የእንግሊዝ ድራማ በማበብ እና እንደ ፍራንሲስ ድሬክ እና ዋልተር ራሌይ ባሉ የእንግሊዝ የባህር ላይ ጀብደኞች ብቃቶች ታዋቂ ነው። አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች ኤልዛቤትን እንደ አጭር ግልፍተኛ፣ አንዳንዴም ቆራጥ የሆነች ገዥ አድርገው ይገልጻሉ፣ ከእርስዋ ትክክለኛ የዕድል ድርሻ በላይ የምትደሰት። በንግሥናዋ መገባደጃ አካባቢ፣ ተከታታይ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ችግሮች ተወዳጅነቷን አዳከሙ። ነገር ግን፣ ኤልዛቤት እንደ ገሪዝማቲክ ተዋናይ እና ውሾች በህይወት የተረፈች በነበረበት ዘመን መንግስት በተጨናነቀ እና ውስን በሆነበት እና በአጎራባች ሀገራት ያሉ ነገስታት ዙፋኖቻቸውን አደጋ ላይ የሚጥሉ የውስጥ ችግሮች ሲያጋጥሟቸው ነው። ከግማሽ ወንድሞቿ እና እህቶቿ አጭር የግዛት ዘመን በኋላ፣ በዙፋኑ ላይ ያሳለፉት 44 ዓመታት ለመንግሥቱ መረጋጋትን አስገኝተው ብሔራዊ ማንነት እንዲገነዘቡ ረድተዋል። የመጀመሪያ ህይወት ኤልዛቤት በሴፕቴምበር 7 1533 በግሪንዊች ቤተመንግስት የተወለደች ሲሆን በአያቶቿ በዮርክ ኤልዛቤት እና በሌዲ ኤልዛቤት ሃዋርድ ስም ተሰየመች። እሷ ከልጅነቷ ለመዳን በጋብቻ የተወለደችው የእንግሊዙ ሄንሪ ስምንተኛ ሁለተኛ ልጅ ነበረች። እናቷ የሄንሪ ሁለተኛ ሚስት አን ቦሊን ነበረች። ስትወለድ ኤልዛቤት የእንግሊዝ ዙፋን ወራሽ ነበረች። ሄንሪ ወንድ ወራሽ ለመምሰል እና የቱዶርን ተተኪነት ለማረጋገጥ በማሰብ ከማርያም እናት ካትሪን ከአራጎን ጋር ትዳሩን ሲያፈርስ ታላቅ እህቷ ማርያም የሕጋዊ ወራሽነት ቦታ አጥታ ነበር። ሴፕቴምበር 1533 እና የእርሷ አምላክ ወላጆች የካንተርበሪ ሊቀ ጳጳስ ቶማስ ክራንመር ነበሩ; ሄንሪ ኮርቴናይ, 1 ኛ ማርከስ ኦቭ ኤክሰተር; ኤልዛቤት ስታፎርድ, የኖርፎልክ ዱቼዝ; እና ማርጋሬት ዎቶን፣ ዶዋገር ማርሽዮነስ ኦፍ ዶርሴት። በአጎቷ ጆርጅ ቦሊን ፣ ቪስካውንት ሮችፎርድ በሕፃኑ ላይ በተከበረው ሥነ ሥርዓት ላይ አንድ ሽፋን ተደረገ ። ጆን , የስሌፎርድ 1 ኛ ባሮን ሁሴ; ጌታ ቶማስ ሃዋርድ; እና ዊልያም ሃዋርድ፣ 1ኛ ባሮን ሃዋርድ የኤፊንጋም። የአራጎን ካትሪን በተፈጥሮ ምክንያት ከሞተች ከአራት ወራት በኋላ እናቷ በግንቦት 19 ቀን 1536 አንገቷ ተቆርጦ ኤልዛቤት የሁለት አመት ከስምንት ወር ልጅ ነበረች። ኤልዛቤት ህጋዊ እንዳልሆነ ተፈርጆ ነበር እና በንጉሣዊው ተተኪነት ቦታዋን ተነፍጓል። ንግሥት ጄን የዙፋኑ አልጋ ወራሽ የሆነው ልጃቸው ኤድዋርድ በተወለደ ብዙም ሳይቆይ በሚቀጥለው ዓመት ሞተች። ኤልሳቤጥ በጥምቀት በዓል ወቅት ክርስቶስን ወይም የጥምቀትን ጨርቅ ይዛ በወንድሟ ቤተሰብ ውስጥ ትቀመጥ ነበር።የኤልዛቤት የመጀመሪያዋ አስተዳዳሪ ማርጋሬት ብራያን “በህይወቴ ውስጥ የማውቀውን ያህል ለሕፃን እና ለሁኔታዎች ጨዋ ነች” በማለት ጽፋለች። ካትሪን ቻምፐርኖውኔ ፣ በኋላ በእሷ የምትታወቅ ፣ ካትሪን “ካት” አሽሊ ያገባች ፣ በ 1537 የኤልዛቤት አስተዳዳሪ ሆና ተሾመች እና በ 1565 እስክትሞት ድረስ የኤልዛቤት ጓደኛ ሆና ቆይታለች። . በ1544 ዊልያም ግሪንዳል ሞግዚቷ በሆነበት ጊዜ ኤልዛቤት እንግሊዘኛ፣ ላቲን እና ጣሊያንኛ መጻፍ ችላለች። ጎበዝ እና ጎበዝ ሞግዚት በሆነችው ስር እሷም በፈረንሳይኛ እና በግሪክኛ እድገት አሳይታለች። በ12 ዓመቷ የእንጀራ እናቷን ካትሪን ፓረርን የሃይማኖት ሥራ ጸሎቶችን ወይም ሜዲቴሽን ከእንግሊዝኛ ወደ ጣሊያንኛ፣ ላቲን እና ፈረንሳይኛ መተርጎም ችላለች፣ ይህም ለአባቷ እንደ አዲስ ዓመት ስጦታ ያቀረበችለትን ነው። በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ ከነበረችበት ጊዜ ጀምሮ እና በህይወቷ ሙሉ በላቲን እና በግሪክ የበርካታ ክላሲካል ደራሲያን ስራዎችን ተርጉማለች፣የሲሴሮ ፕሮ ማርሴሎ፣ የቦይቲየስ ደ መጽናኛ ፍልስፍና፣ የፕሉታርክ ድርሰት እና የታሲተስ አናልስን ጨምሮ። በዘመናዊው ዘመን ከነበሩት አራት የእንግሊዝኛ ትርጉሞች መካከል አንዱ የሆነው ከላምቢት ቤተ መንግሥት ቤተ መፃህፍት የታሲተስ ትርጉም በ2019 የኤልዛቤት የራሷ እንደሆነ ተረጋግጧል፣ የእጅ ጽሁፍ እና ወረቀት ላይ ዝርዝር ትንታኔ ከተሰጠ በኋላ። በ1548 ግሪንዳል ከሞተች በኋላ፣ ኤልዛቤት ትምህርቷን በወንድሟ ኤድዋርድ አስተማሪ ሮጀር አስቻም ፣ መማር መሳተፊያ መሆን እንዳለበት በማመን አዛኝ አስተማሪ ተቀበለች። አሁን ያለው የኤልዛቤት ትምህርት እና ቅድመ-ትምህርት እውቀት በአብዛኛው የመጣው ከአስቻም ትውስታዎች ነው። በ1550 መደበኛ ትምህርቷ ሲያልቅ፣ ኤልዛቤት በትውልዷ ውስጥ ካሉት ምርጥ የተማሩ ሴቶች አንዷ ነበረች። በህይወቷ መጨረሻ ላይ ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ የዌልስ፣ ኮርኒሽ፣ ስኮትላንዳዊ እና አይሪሽ ቋንቋዎችን እንደምትናገር ታምኖ ነበር። የቬኒስ አምባሳደር በ1603 “[እነዚህን] ቋንቋዎች በሚገባ ስለያዘች እያንዳንዳቸው የአፍ መፍቻ ቋንቋዋ እስኪመስሉ ድረስ” ተናግራለች። የታሪክ ምሁሩ ማርክ ስቶይል ምናልባት ኮርኒሽኛን በዊልያም ኪሊግሬው፣ የፕራይቪ ቻምበር ሙሽራ እና በኋላም ቻምበርሊን ኦቭ ዘ ኤክስቼከር እንዳስተማራት ጠቁመዋል።የኤልዛቤት የመጀመሪያዋ አስተዳዳሪ ማርጋሬት ብራያን “በህይወቴ ውስጥ የማውቀውን ያህል ለሕፃን እና ለሁኔታዎች ጨዋ ነች” በማለት ጽፋለች። ካትሪን ቻምፐርኖውኔ ፣ በኋላ በእሷ የምትታወቅ ፣ ካትሪን “ካት” አሽሊ ያገባች ፣ በ 1537 የኤልዛቤት አስተዳዳሪ ሆና ተሾመች እና በ 1565 እስክትሞት ድረስ የኤልዛቤት ጓደኛ ሆና ቆይታለች። . በ1544 ዊልያም ግሪንዳል ሞግዚቷ በሆነበት ጊዜ ኤልዛቤት እንግሊዘኛ፣ ላቲን እና ጣሊያንኛ መጻፍ ችላለች። ጎበዝ እና ጎበዝ ሞግዚት በሆነችው ስር እሷም በፈረንሳይኛ እና በግሪክኛ እድገት አሳይታለች። በ12 ዓመቷ የእንጀራ እናቷን ካትሪን ፓረርን የሃይማኖት ሥራ ጸሎቶችን ወይም ሜዲቴሽን ከእንግሊዝኛ ወደ ጣሊያንኛ፣ ላቲን እና ፈረንሳይኛ መተርጎም ችላለች፣ ይህም ለአባቷ እንደ አዲስ ዓመት ስጦታ ያቀረበችለትን ነው። በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ ከነበረችበት ጊዜ ጀምሮ እና በህይወቷ ሙሉ በላቲን እና በግሪክ የበርካታ ክላሲካል ደራሲያን ስራዎችን ተርጉማለች፣የሲሴሮ ፕሮ ማርሴሎ፣ የቦይቲየስ ደ መጽናኛ ፍልስፍና፣ የፕሉታርክ ድርሰት እና የታሲተስ አናልስን ጨምሮ። በዘመናዊው ዘመን ከነበሩት አራት የእንግሊዝኛ ትርጉሞች መካከል አንዱ የሆነው ከላምቢት ቤተ መንግሥት ቤተ መፃህፍት የታሲተስ ትርጉም በ2019 የኤልዛቤት የራሷ እንደሆነ ተረጋግጧል፣ የእጅ ጽሁፍ እና ወረቀት ላይ ዝርዝር ትንታኔ ከተሰጠ በኋላ። በ1548 ግሪንዳል ከሞተች በኋላ፣ ኤልዛቤት ትምህርቷን በወንድሟ ኤድዋርድ አስተማሪ ሮጀር አስቻም ፣ መማር መሳተፊያ መሆን እንዳለበት በማመን አዛኝ አስተማሪ ተቀበለች። አሁን ያለው የኤልዛቤት ትምህርት እና ቅድመ-ትምህርት እውቀት በአብዛኛው የመጣው ከአስቻም ትውስታዎች ነው። በ1550 መደበኛ ትምህርቷ ሲያልቅ፣ ኤልዛቤት በትውልዷ ውስጥ ካሉት ምርጥ የተማሩ ሴቶች አንዷ ነበረች። በህይወቷ መጨረሻ ላይ ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ የዌልስ፣ ኮርኒሽ፣ ስኮትላንዳዊ እና አይሪሽ ቋንቋዎችን እንደምትናገር ታምኖ ነበር። የቬኒስ አምባሳደር በ1603 “[እነዚህን] ቋንቋዎች በሚገባ ስለያዘች እያንዳንዳቸው የአፍ መፍቻ ቋንቋዋ እስኪመስሉ ድረስ” ተናግራለች። የታሪክ ምሁሩ ማርክ ስቶይል ምናልባት ኮርኒሽኛን በዊልያም ኪሊግሬው፣ የፕራይቪ ቻምበር ሙሽራ እና በኋላም ቻምበርሊን ኦቭ ዘ ኤክስቼከር እንዳስተማራት ጠቁመዋል። ቶማስ ሲይሞር ሄንሪ ስምንተኛ በ1547 ሞተ እና የኤልዛቤት ግማሽ ወንድም ኤድዋርድ ስድስተኛ በ9 ዓመቱ ንጉስ ሆነ። የሄንሪ መበለት ካትሪን ፓር ብዙም ሳይቆይ ቶማስ ሲይሞርን፣ የሱዴሊ 1ኛ ባሮን ሲይሞርን፣ የኤድዋርድ ስድስተኛ አጎት እና የሎርድ ጠበቃ ኤድዋርድ ሲይሞርን ወንድም፣ የሱመርሴት 1 መስፍንን አገባች። ጥንዶቹ ኤልዛቤትን ወደ ቼልሲ ቤታቸው ወሰዱ። እዚያም ኤልዛቤት አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች በቀሪው ሕይወቷ እንደነካት የሚያምኑትን የስሜት ቀውስ አጋጥሟታል። ቶማስ ሲሞር ከ14 ዓመቷ ኤልዛቤት ጋር በፈረስ ግልቢያ እና የሌሊት ልብሱን ለብሳ ወደ መኝታ ቤቷ መግባቱን፣ መኳኳትን እና ቂጥ ላይ በጥፊ መምታት ጨምሮ ነበር። ኤልዛቤት በማለዳ ተነሳች እና ያልተፈለገ የጠዋት ጉብኝቶችን ለማስቀረት እራሷን በገረዶች ከበበች። ፓር ባሏን ተገቢ ባልሆነ እንቅስቃሴው ከመጋፈጥ ይልቅ ተቀላቀለች። ሁለት ጊዜ ኤልዛቤትን ስትመታ አብራው ነበር፣ እና አንድ ጊዜ ጥቁር ጋዋንዋን "በሺህ ቁርጥራጮች" ቆርጦ ያዘቻት። ሆኖም፣ ፓር ጥንዶቹን በእቅፍ ካገኛት በኋላ፣ ይህንን ሁኔታ ጨርሳለች። በግንቦት 1548 ኤልዛቤት ተባረረች። ቶማስ ሲይሞር ግን የንጉሣዊ ቤተሰብን ለመቆጣጠር ማሴሩን ቀጠለ እና የንጉሱን ሰው ገዥ ለመሾም ሞከረ። ፓር በሴፕቴምበር 5 1548 ከወሊድ በኋላ ሲሞት፣ እሷን ለማግባት በማሰብ ትኩረቱን ወደ ኤልዛቤት አድሷል። ሴይሞርን የምትወደው አስተዳዳሪዋ ካት አሽሊ ኤልዛቤት እሱን እንደ ባሏ እንድትወስድ ለማሳመን ፈለገች። እሷም ኤልዛቤትን ለሴይሞር እንድትጽፍ እና “በሀዘኑም እንድታጽናናው” ለማሳመን ሞክራለች፣ ነገር ግን ኤልዛቤት ቶማስ በእንጀራ እናቷ ሞት እንዳሳዘነች ተናግራ መጽናኛ እንደፈለገች ተናግራለች። በጥር 1549 ሲይሞር ወንድሙን ሱመርሴትን ከተከላካይነት ለማውረድ፣ ሌዲ ጄን ግሬይን ለንጉስ ኤድዋርድ 6ኛ ለማግባት እና ኤልዛቤትን እንደ ራሷ ሚስት ለማድረግ በማሴር ተጠርጥሮ ተይዞ በግንቡ ውስጥ ታስሯል። በ ሃትፊልድ ሃውስ የምትኖረው ኤልዛቤት ምንም አትቀበልም። ግትርነቷ ጠያቂዋን ሰር ሮበርት ቲርዊትን “ጥፋተኛ መሆኗን በፊቷ አይቻለሁ” ሲሉ ዘግበውታል። ሲይሞር መጋቢት 20 ቀን 1549 አንገቱ ተቆረጠ ንግስና ማርያም ኤድዋርድ ስድስተኛ በጁላይ 6 1553 በ15 ዓመቱ አረፈ። ኑዛዜው የ1543 የዘውድ ሥልጣንን ቸል በማለት ማርያምን እና ኤልዛቤትን ተተኪነት አገለለ እና በምትኩ የሄንሪ ስምንተኛ ታናሽ እህት የማርያም የልጅ ልጅ የሆነችውን ሌዲ ጄን ግሬይ ወራሽ አድርጎ ገልጿል። ጄን በፕራይቪ ካውንስል ንግሥት ተባለች፣ ነገር ግን ድጋፏ በፍጥነት ፈራረሰ፣ እና ከዘጠኝ ቀናት በኋላ ከስልጣን ተባረረች። እ.ኤ.አ. ኦገስት 3 1553 ማርያም በድል አድራጊነት ወደ ለንደን ገባች፣ ኤልዛቤትም ከጎኗ ነበር።በእህቶች መካከል ያለው የአብሮነት ትርኢት ብዙም አልዘለቀም። አጥባቂ ካቶሊክ የነበረችው ሜሪ ኤልዛቤት የተማረችበትን የፕሮቴስታንት እምነት ለማጥፋት ቆርጣ ተነስታ ሁሉም ሰው በካቶሊክ ቅዳሴ ላይ እንዲገኝ አዘዘች። ኤልዛቤት በውጫዊ ሁኔታ መስማማት ነበረባት። የማርያም የመጀመሪያ ተወዳጅነት በ 1554 የቅዱስ ሮማዊው ንጉሠ ነገሥት ቻርልስ አምስተኛ ልጅ እና ንቁ የካቶሊክ እምነት ተከታይ የሆነውን ስፔናዊውን ፊሊፕ ለማግባት ማቀዷን ስታስታውቅ ነበር። ብስጭት በአገሪቱ በፍጥነት ተሰራጭቷል፣ እና ብዙዎች የማርያምን ሃይማኖታዊ ፖሊሲዎች በመቃወም ኤልዛቤትን እንደ ትኩረት አድርገው ይመለከቱ ነበር። በጥር እና በፌብሩዋሪ 1554 የዋይት አመጽ ተነሳ; ብዙም ሳይቆይ ታፍኗል። ኤልዛቤት ፍርድ ቤት ቀርቦ ስለእሷ ሚና ተጠይቃለች፣ እና በመጋቢት 18፣ በለንደን ግንብ ውስጥ ታስራለች። ኤልዛቤት ንፁህነቷን አጥብቃ ተቃወመች። ምንም እንኳን ከዓመፀኞቹ ጋር ማሴር ባትችልም አንዳንዶቹ ወደ እርሷ እንደቀረቡ ይታወቃል። የማርያም የቅርብ ታማኝ፣ የቻርልስ አምስተኛ አምባሳደር ሲሞን ሬናርድ፣ ኤልዛቤት በምትኖርበት ጊዜ ዙፋኗ መቼም ቢሆን ደህና አይሆንም ሲል ተከራከረ። እና ሎርድ ቻንስለር እስጢፋኖስ ጋርዲነር፣ ኤልዛቤት ለፍርድ እንድትቀርብ ሠርተዋል። በመንግስት ውስጥ ያሉ የኤልዛቤት ደጋፊዎች፣ ዊልያም ፔጅን፣ 1ኛ ባሮን ፔጅትን ጨምሮ፣ በእሷ ላይ ጠንካራ ማስረጃ በሌለበት ማርያም እህቷን እንድትታደግ አሳመኗት። በምትኩ፣ በግንቦት 22፣ ኤልዛቤት ከግንቡ ወደ ዉድስቶክ ተዛወረች፣ እዚያም በሰር ሄንሪ ቤዲንግፌልድ ክስ ውስጥ ለአንድ አመት ያህል በቤት እስራት ልታሳልፍ ነበር። ህዝቡ በመንገዱ ሁሉ ደስ አሰኝቷታል።እ.ኤ.አ. ኤፕሪል 17 ቀን 1555 ኤልዛቤት የማርያምን ግልፅ እርግዝና የመጨረሻ ደረጃ ላይ ለመገኘት ወደ ፍርድ ቤት ተጠራች። ማርያምና ​​ልጇ ቢሞቱ ኤልሳቤጥ ንግሥት ትሆናለች፣ነገር ግን ማርያም ጤናማ ልጅ ከወለደች፣ የኤልሳቤጥ ንግሥት የመሆን እድሏ በጣም እያሽቆለቆለ ይሄዳል። ማርያም እንዳልፀነሰች ሲታወቅ ልጅ መውለድ እንደምትችል ማንም አላመነም። የኤልዛቤት ተተኪነት የተረጋገጠ ይመስላል። በ1556 የስፔን ዙፋን ላይ የወጣው ንጉስ ፊሊፕ አዲሱን የፖለቲካ እውነታ አምኖ አማቱን አሳደገ። በፈረንሳይ ያደገችው እና ከፈረንሳይ ዳፊን ጋር ከታጨችው ከዋነኛው አማራጭ ሜሪ፣ የስኮትላንዳዊቷ ንግሥት የተሻለ አጋር ነበረች። በ1558 ሚስቱ ስትታመም ንጉስ ፊልጶስ ከኤልሳቤጥ ጋር ለመመካከር የፌሪያን ግዛት ላከ። ይህ ቃለ ምልልስ የተካሄደው በጥቅምት 1555 ለመኖር በተመለሰችው ሃትፊልድ ሃውስ ነው። በጥቅምት 1558 ኤልዛቤት ለመንግሥቷ እቅድ አውጥታ ነበር። ማርያም ህዳር 6 ቀን 1558 ኤልዛቤትን እንደ ወራሽ አወቀች፣ እና ኤልሳቤጥ ንግሥት ሆና በኖቬምበር 17 ማርያም ስትሞት ኤልሳቤጥ በ25 ዓመቷ ንግሥት ሆነች፣ እና ፍላጎቷን ለምክር ቤትዋ እና ሌሎች ጓደኞቿን ታማኝ ለመሆን ወደ ሃትፊልድ ለመጡት ተናገረች። ንግግሩ የሉዓላዊውን "ሁለት አካላት" የመካከለኛው ዘመን የፖለቲካ ሥነ-መለኮትን የተቀበለችበትን የመጀመሪያ ዘገባ ይዟል፡ አካል ተፈጥሯዊ እና ፖለቲካዊ፡ ጌቶቼ፣ የተፈጥሮ ህግ ለእህቴ እንዳዝን ያነሳሳኛል; በእኔ ላይ የወረደው ሸክም አስገረመኝ፣ ነገር ግን እኔ የእግዚአብሔር ፍጡር እንደ ሆንኩ በመቁጠር፣ ሹመቱን እንድፈጽም የተሾምኩ፣ ለዚያም እሺ እሆናለሁ፣ አገልጋይ ለመሆን የጸጋውን እርዳታ ለማግኘት ከልቤ እመኛለሁ። በዚህ ቢሮ ውስጥ ስላለው ሰማያዊ ፈቃዱ አሁን ለእኔ የተሰጠኝ። እኔ በተፈጥሮ አንድ አካል እንደ ሆንሁ፥ ምንም እንኳን በእርሱ ፈቃድ አንድ የፖለቲካ አካል ለመምራት፥ ሁላችሁንም ... በእኔ ፍርድ እናንተም ከእናንተ አገልግሎት ጋር በመልካም ሒሳብ እንድትሰጡኝ ረዳቱ ትሆኑ ዘንድ እፈቅዳለሁ። ለልዑል እግዚአብሔር እና በምድር ላይ ላሉ ዘመዶቻችን አንዳንድ መጽናናትን ይተውልን። ሁሉንም ድርጊቶቼን በጥሩ ምክር እና ምክር መምራት ማለቴ ነው። በዘውድ ሥርዓቱ ዋዜማ የድል ግስጋሴዋ በከተማዋ ሲታመስ፣ በዜጎች በሙሉ ልቧ የተቀበሏት እና በንግግሮች እና ትርኢቶች የተቀበሏት እጅግ በጣም ጠንካራ የፕሮቴስታንት ጣእም ያለው ነው። የኤልዛቤት ግልጽ እና የጸጋ ምላሽ ሰጪዎች “በድንቅ የተደፈሩ” ተመልካቾችን እንድትወድ አድርጓታል። በማግስቱ፣ ጥር 15 ቀን 1559፣ በኮከብ ቆጣሪዋ ጆን ዲ፣ ኤልዛቤት የተመረጠችበት ቀን በዌስትሚኒስተር አቢ በካርሊል የካቶሊክ ጳጳስ ኦወን ኦግሌቶርፕ ዘውድ ተቀዳጀች። ከዚያም ሰዎቹ እንዲቀበሏት ቀረበች፣ በሚሰሙት የአካል ክፍሎች፣ ፊፋ፣ ጥሩምባ፣ ከበሮ እና ደወሎች መካከል። ምንም እንኳን ኤልዛቤት በእንግሊዝ ንግሥት ሆና እንኳን ደህና መጣችሁ ብትልም፣ ሀገሪቱ አሁንም በሃገር ውስጥ እና በባህር ማዶ የሚደርሰው የካቶሊክ ስጋት፣ እንዲሁም ማንን እንደምታገባ በመምረጡ ስጋት ላይ ነች። የቤተክርስቲያን ሰፈር የኤልዛቤት የግል ሃይማኖታዊ እምነቶች በሊቃውንት ብዙ ክርክር ተደርጎባቸዋል። እሷ ፕሮቴስታንት ነበረች፣ ነገር ግን የካቶሊክ ምልክቶችን (እንደ ስቅለት ያሉ) ትይዛለች፣ እና የፕሮቴስታንት ቁልፍ የሆነውን እምነት በመቃወም የስብከትን ሚና አሳንሳለች። ኤልዛቤት እና አማካሪዎቿ በመናፍቃን እንግሊዝ ላይ የካቶሊክ የመስቀል ጦርነት እንደሚያስፈራራ ተገነዘቡ። ስለዚህ ንግስቲቱ የእንግሊዝ ፕሮቴስታንቶችን ፍላጎት እየተናገረች ካቶሊኮችን በእጅጉ የማያስከፋ ፕሮቴስታንት መፍትሄ ፈለገች፣ነገር ግን ሰፊ ተሃድሶ እንዲደረግ የሚገፋፉትን ፒዩሪታኖችን አትታገስም። በዚህ ምክንያት የ1559 ፓርላማ በኤድዋርድ ስድስተኛ ፕሮቴስታንት ሰፈር ላይ የተመሰረተ ቤተክርስትያን ንጉሱ ራስ ሆኖ ነገር ግን እንደ አልባሳት ያሉ ብዙ የካቶሊክ አካላት ላሉት ቤተክርስቲያን ህግ ማውጣት ጀመረ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀሳቦቹን አጥብቆ ደግፏል፣ ነገር ግን የላዕላይነት ረቂቅ ህግ በጌቶች ምክር ቤት በተለይም ከጳጳሳት ተቃውሞ ገጠመው። የካንተርበሪ ሊቀ ጳጳስ ጨምሮ ብዙ ጳጳሳት በወቅቱ ክፍት በመሆናቸው ኤልዛቤት እድለኛ ነበረች። ቢሆንም፣ ብዙዎች አንዲት ሴት ለመሸከም ተቀባይነት እንደሌለው በማሰብ ኤልዛቤት ይበልጥ አከራካሪ ከሆነው የበላይ አለቃ ይልቅ የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ገዥ የሚለውን ማዕረግ ለመቀበል ተገድዳለች። በግንቦት 8 ቀን 1559 አዲሱ የበላይነት ህግ ህግ ሆነ። ሁሉም የመንግስት ባለስልጣናት ለንጉሱ የበላይ ገዥ በመሆን ታማኝነታቸውን መማል ወይም ከስልጣን መባረር አለባቸው። በማርያም ይፈጸም የነበረው ተቃዋሚዎች ስደት እንዳይደገም የኑፋቄ ሕጎቹ ተሽረዋል። በተመሳሳይ ጊዜ፣ ቤተ ክርስቲያን መገኘትን እና የ1552 የጋራ ጸሎት መጽሐፍን በተሻሻለው እትም መጠቀምን የሚያስገድድ አዲስ የወጥነት ሕግ ወጣ፣ ምንም እንኳን በዳግም መቀበል ወይም አለመገኘት እና አለመከተል ቅጣቶች ጽንፍ ባይሆኑም . የጋብቻ ጥያቄ ከኤሊዛቤት ንግሥና መጀመሪያ ጀምሮ ታገባለች ተብሎ ይጠበቅ ነበር, እና ጥያቄው ለማን ተነሳ. ብዙ ቅናሾችን ብታገኝም አላገባችም እና ልጅ አልባ ሆና ቀረች; ለዚህ ምክንያቱ ግልጽ አይደለም. የታሪክ ተመራማሪዎች ቶማስ ሲሞር ከፆታዊ ግንኙነት እንዳቋረጠ ይገምታሉ። ሃምሳ እስክትሆን ድረስ ብዙ ፈላጊዎችን አስባለች። የመጨረሻ የፍቅር ጓደኝነት የ22 ዓመቷ የአንጁው መስፍን ፍራንሲስ ጋር ነበር። በስፔናዊው ንጉስ ፊሊፕ 2ኛ እጅ እንደተጫወተችው እህቷ ስልጣኗን ሊያጣ እንደሚችል ስጋት ውስጥ ገብታለች፣ ትዳር ወራሽ የመሆን እድል ፈጠረላት። ሆኖም የባል ምርጫ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት አልፎ ተርፎም ዓመፅ ያስነሳል። ሮበርት ዱድሊ በ1559 የጸደይ ወራት፣ ኤልዛቤት ከልጅነት ጓደኛዋ ከሮበርት ዱድሊ ጋር ፍቅር እንደነበራት ግልጽ ሆነ። ሚስቱ ኤሚ ሮብሳርት "በአንደኛው ጡቷ ላይ በሚታመም በሽታ" እየተሰቃየች እንደነበረ እና ንግስቲቱ ሚስቱ ብትሞት ዱድሊን ማግባት እንደምትፈልግ ተነግሯል። እጅ; ትዕግሥት የለሽ መልእክቶቻቸው ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ አሳፋሪ ንግግር ውስጥ ተሰማርተው እና ከምትወደው ጋር ጋብቻ በእንግሊዝ ውስጥ ተቀባይነት እንደሌለው ዘግበዋል: - “በእሱ እና በእሷ ላይ በቁጣ የማይጮህ ሰው የለም… እሷ ከተወደዱ በስተቀር ማንንም አታገባም ። ሮበርት." ኤሚ ዱድሊ በሴፕቴምበር 1560 ከደረጃ በረራ ላይ በመውደቁ ሞተች እና ምንም እንኳን የምርመራ ተቆጣጣሪው የአደጋ ምርመራ ቢያገኝም ፣ ብዙ ሰዎች ባሏ ንግሥቲቱን እንዲያገባ ሲል ሞቷን አመቻችቷል ብለው ጠረጠሩት። ኤልዛቤት ዱድሊንን ለተወሰነ ጊዜ ለማግባት አስባ ነበር። ሆኖም ዊልያም ሴሲል፣ ኒኮላስ ትሮክሞርተን እና አንዳንድ ወግ አጥባቂ እኩዮቻቸው አለመስማማታቸውን በማያሻማ መልኩ ግልጽ አድርገዋል። ጋብቻው ከተፈጸመ ባላባቶች እንደሚነሱ የሚነገር ወሬም ነበር። ሮበርት ዱድሊ ለንግስት ተብለው ከሚታሰቡ ሌሎች የጋብቻ እጩዎች መካከል፣ ለሌላ አስርት ዓመታት ያህል እንደ እጩ መቆጠር ቀጠለ። ኤልዛቤት በፍቅሩ በጣም ትቀና ነበር፣ ምንም እንኳን እሷ ራሷ ልታገባው ባትፈልግም ነበር። እ.ኤ.አ. በ1564 ዱድሊንን እንደ የሌስተር አርል አሳደገችው። በመጨረሻም በ 1578 እንደገና አገባ, ንግሥቲቱ ለባለቤቱ ሌቲስ ኖሊስ ተደጋጋሚ ብስጭት እና የዕድሜ ልክ ጥላቻ ምላሽ ሰጥታለች. አሁንም፣ ዱድሊ የታሪክ ምሁር የሆኑት ሱዛን ዶራን ሁኔታውን እንደገለፁት ሁል ጊዜ “[የኤልዛቤት] ስሜታዊ ሕይወት መሃል ላይ ይቆዩ ነበር። እ.ኤ.አ. በ1588 የስፔን ጦር ከተሸነፈ በኋላ ብዙም ሳይቆይ ሞተ። ኤልዛቤት ከሞተች በኋላ፣ በጣም ከግል ንብረቶቿ መካከል ከእርሱ የተላከ ማስታወሻ ተገኘች፤ በእጇ በጻፈችው ጽሑፍ ላይ “የመጨረሻው ደብዳቤ” የውጭ አገር እጩዎች የጋብቻ ድርድር በኤልዛቤት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ውስጥ ቁልፍ አካል ነበር። በ1559 መጀመሪያ ላይ የግማሽ እህቷ ሚስት የነበረችውን የፊሊፕን እጅ አልተቀበለችም ፣ ግን ለብዙ ዓመታት የስዊድን ንጉስ ኤሪክ አሥራ አራተኛውን ሀሳብ አቀረበች። ቀደም ሲል በኤልዛቤት ሕይወት ውስጥ ለእሷ የዴንማርክ ግጥሚያ ውይይት ተደርጎበታል ። ሄንሪ ስምንተኛ በ1545 ከዴንማርክ ልዑል አዶልፍ ፣የሆልስታይን-ጎቶርፕ መስፍን ጋር እና ኤድዋርድ ሲይሞር ፣የሱመርሴት መስፍን ከፕሪንስ ፍሬድሪክ (በኋላ ፍሬደሪክ 2) ከበርካታ አመታት በኋላ እንዲጋቡ ሀሳብ አቅርበው ነበር ፣ነገር ግን ድርድሩ በ1551 ቀነሰ እ.ኤ.አ. በ1559 አካባቢ የዳኖ-እንግሊዘኛ ፕሮቴስታንት ህብረት ታሳቢ ተደርጎ ነበር፣ እና የስዊድንን ሃሳብ ለመቃወም ንጉስ ፍሬድሪክ በ1559 መጨረሻ ላይ ለኤልዛቤት ጥያቄ አቀረበ።ለብዙ አመታት እሷም የፊሊፕን የአጎት ልጅ ቻርልስ ፣ የኦስትሪያውን አርክዱክን ለማግባት በቁም ነገር ተደራድራለች። እ.ኤ.አ. በ 1569 ከሀብስበርግ ጋር ያለው ግንኙነት ተበላሽቷል ። ኤልዛቤት በተራው ከሁለት የፈረንሣይ ቫሎይስ መኳንንት ጋር ጋብቻን አስባ ነበር ፣ በመጀመሪያ ሄንሪ ፣ የአንጁዱ መስፍን ፣ እና ከ 1572 እስከ 1581 ወንድሙ ፍራንሲስ ፣ የአንጁው መስፍን ፣ የቀድሞ የአሌንኮን መስፍን። ይህ የመጨረሻው ሀሳብ በደቡባዊ ኔዘርላንድ የስፔን ቁጥጥር ላይ ከታቀደው ጥምረት ጋር የተያያዘ ነው። ኤልዛቤት የፍቅር ጓደኝነትን ለተወሰነ ጊዜ በቁም ​​ነገር የወሰደችው እና ፍራንሲስ የላከላትን የእንቁራሪት ቅርጽ ያለው የጆሮ ጌጥ ለብሳለች። እ.ኤ.አ. በ 1563 ኤልዛቤት የንጉሠ ነገሥቱን ልዑክ “የተፈጥሮዬን ዝንባሌ ከተከተልኩ ይህ ነው-ለማኝ ሴት እና ነጠላ ፣ ከንግሥት እና ከጋብቻ ይልቅ። በዓመቱ በኋላ፣ ኤልዛቤት በፈንጣጣ መታመሟን ተከትሎ፣ የመተካካት ጥያቄ በፓርላማ ውስጥ የጦፈ ጉዳይ ሆነ። አባላት ንግስቲቱ እንድትጋባ ወይም ወራሽ እንድትሰይም አሳስቧታል፣ ስትሞት የእርስ በርስ ጦርነትን ለመከላከል። እሷም ለማድረግ ፈቃደኛ አልሆነችም። በ 1566 ታክስ ለመጨመር ድጋፉን እስክትፈልግ ድረስ እንደገና ያልተሰበሰበውን ፓርላማ በኤፕሪል አነሳች ። ከዚህ ቀደም ለማግባት ቃል ገብታ፣ ሥርዓት ለሌለው ቤት እንዲህ አለች፡-ለክብር ስል በአደባባይ የተነገረውን የልዑል ቃል በፍጹም አላፈርስም። ስለዚህም ደግሜ እላለሁ፣ በተመቸኝ መጠን አገባለሁ፣ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ላገባው የምፈልገውን ወይም ራሴን ካልወሰደው፣ ወይም ሌላ ታላቅ ነገር ቢፈጠር። እ.ኤ.አ. በ 1570 በመንግስት ውስጥ ያሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ኤልዛቤት በጭራሽ አታገባም ወይም ተተኪ አትሰይም ብለው በግል ተቀበሉ። ዊልያም ሴሲል ቀድሞውንም ለተከታታይ ችግር መፍትሄዎችን እየፈለገ ነበር። ኤልዛቤት ባለማግባቷ ብዙ ጊዜ በኃላፊነት የጎደለው ድርጊት ትከሰሳለች። ዝምታዋ ግን የራሷን የፖለቲካ ደህንነት አጠንክሯል፡ ወራሽ ብትሰይም ዙፋንዋ ለየግል ግልበጣ እንደሚጋለጥ ታውቃለች። "እንደ እኔ ሁለተኛ ሰው" በቀድሞዋ ላይ የሴራዎች ትኩረት የተደረገበትን መንገድ አስታውሳለች. የኤልዛቤት ያላገባች ሁኔታ ከድንግል ማርያም ጋር የተያያዘ የድንግልና አምልኮን አነሳሳ። በግጥም እና በቁም ሥዕላዊ መግለጫ፣ እርሷ በድንግልና፣ አምላክ ወይም ሁለቱም ተመስላለች እንጂ እንደ መደበኛ ሴት አይታይም። መጀመሪያ ላይ ኤልሳቤጥ ብቻ የድንግልናዋን መልካም ነገር አደረገች፡ በ1559 ለጋራ ማህበረሰብ እንዲህ አለች፡- “እናም፣ በመጨረሻ፣ ይህ ይበቃኛል፣ የእብነበረድ ድንጋይ ንግሥት እንዲህ ያለ ጊዜ እንደነገሠች ያስታውቃል። በድንግልና ኖረች ሞተችም። በኋላ፣ ገጣሚዎች እና ጸሃፊዎች ጭብጡን አነሱ እና ኤልዛቤትን ከፍ ያደረገችውን ምስል አዘጋጁ። እ.ኤ.አ. በ 1578 ለድንግል የተሰጡ የህዝብ ውለታዎች ንግሥቲቱ ከአሌንኮን መስፍን ጋር ባደረገችው የጋብቻ ድርድር ላይ የተቃውሞ ኮድ ማረጋገጫ ሆኖ አገልግሏል። በመጨረሻ፣ ኤልዛቤት በመለኮታዊ ጥበቃ ስር ከግዛቷ እና ከተገዥዎቿ ጋር እንዳገባች አጥብቃ ትጠይቃለች። በ 1599 ስለ "ባሎቼ ሁሉ, የእኔ ጥሩ ሰዎች" ተናገረች.ይህ የድንግልና ይገባኛል ጥያቄ በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት አላገኘም። ካቶሊኮች ኤልዛቤትን ከሰውነቷ ጋር በምሳሌያዊ ሁኔታ የሚያረክሰውን “ርኩስ ፍትወት” ውስጥ ገብታለች ሲሉ ከሰሷት። ፈረንሳዊው ሄንሪ አራተኛ የአውሮፓ ታላላቅ ጥያቄዎች አንዱ "ንግሥት ኤልሳቤጥ ገረድ ነበረች ወይስ አይደለም" የሚለው ነው። የኤልዛቤት ድንግልና ጥያቄን በተመለከተ ዋናው ጉዳይ ንግስቲቱ ከሮበርት ዱድሊ ጋር የነበራትን የፍቅር ግንኙነት ፈጽማለች ወይ የሚለው ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1559 የዱድሊ መኝታ ቤቶች ከራሷ አፓርታማዎች አጠገብ እንዲዛወሩ አደረገች። እ.ኤ.አ. በ1561 ሰውነቷ እንዲያብጥ ባደረገው ህመም ሚስጥራዊ በሆነ መልኩ የአልጋ ቁራኛ ሆናለች። በ1587 ራሱን አርተር ዱድሌይ ብሎ የሚጠራ ወጣት በስፔን የባህር ዳርቻ በሰላዩ ተጠርጥሮ ተይዟል። ሰውዬው የኤልዛቤት እና የሮበርት ዱድሌይ ህገወጥ ልጅ ነኝ ሲል በ1561 በህመም ወቅት ከልደቱ ጋር የሚስማማ እድሜው ነበር። ለምርመራ ወደ ማድሪድ ተወሰደ፣ እዚያም ወደ ስፔን በግዞት በተወሰደው የካቶሊክ መኳንንት እና የንጉስ ፊሊፕ 2ኛ ፀሃፊ በሆነው ፍራንሲስ ኢንግልፊልድ ተመርምሯል። አርተር በንጉሣዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ ከተወለደበት ጊዜ አንስቶ ወደ ስፔን እስከሚደርስበት ጊዜ ድረስ የሕይወቱ ታሪክ መሆኑን የሚገልጹ ሦስት ደብዳቤዎች ቃለ-መጠይቁን የሚገልጹ ሦስት ደብዳቤዎች ዛሬ አሉ። ሆኖም ይህ ስፔናዊውን ማሳመን አልቻለም፡ ኢንግፊልድ የአርተር “አሁን ያለው የይገባኛል ጥያቄ ምንም አይደለም” ሲል ለንጉስ ፊሊፕ አምኗል፣ ነገር ግን “እንዲሸሽ መፍቀድ የለበትም፣ ነገር ግን በጣም ደህንነቱ የተጠበቀ ነው” ሲል ጠቁሟል። ንጉሱ ተስማምተው ነበር፣ እና አርተር ከአሁን በኋላ አልተሰማም። የዘመናችን ስኮላርሺፕ የታሪኩን መሰረታዊ መነሻ “የማይቻል” በማለት ውድቅ አድርጎታል እና የኤልዛቤት ህይወት በዘመኗ በነበሩ ሰዎች በጣም በቅርብ ይታይ ስለነበር እርግዝናን መደበቅ አልቻለችም ሲል ተናግሯል። የስኮትስ ንግሥት ማርያም በስኮትላንድ ላይ የኤሊዛቤት የመጀመሪያ ፖሊሲ የፈረንሳይን መኖር መቃወም ነበር። ፈረንሳዮች እንግሊዝን ለመውረር እንዳቀዱ እና የካቶሊክ ዘመድ የሆነችውን የስኮትላንድ ንግሥት ማርያምን በዙፋኑ ላይ እንዳስቀምጧት ፈራች። ሜሪ የሄንሪ ስምንተኛ ታላቅ እህት ማርጋሬት የልጅ ልጅ በመሆኗ የእንግሊዝ ዘውድ ወራሽ እንደሆነች ብዙዎች ይቆጠሩ ነበር። ማርያም “የቅርብ ዘመድ ያላት ሴት” በመሆኗ በኩራት ተናግራለች። ኤልዛቤት የፕሮቴስታንት አማፂያንን ለመርዳት ወደ ስኮትላንድ ጦር እንድትልክ ተገፋፍታ ነበር፣ እና ዘመቻው የተሳሳተ ቢሆንም፣ በጁላይ 1560 የወጣው የኤድንበርግ ስምምነት የፈረንሳይን ስጋት በሰሜን በኩል አስወገደ።[] ሜሪ በ1561 ወደ ስኮትላንድ ስትመለስ በስልጣን ላይ ሀገሪቱ የተመሰረተች የፕሮቴስታንት ቤተክርስትያን ነበራት እና የምትመራው በኤሊዛቤት ድጋፍ በፕሮቴስታንት መኳንንት ምክር ቤት ነበር። ማርያም ስምምነቱን ለማጽደቅ ፈቃደኛ አልሆነችም። እ.ኤ.አ. በ 1563 ኤልዛቤት የራሷን ፈላጊ ሮበርት ዱድሊን ለማርያም ባል እንድትሆን አቀረበች ፣ የሚመለከታቸውን ሁለት ሰዎች ሳትጠይቅ ። ሁለቱም ደስተኞች አልነበሩም እና በ 1565 ሜሪ ሄንሪ ስቱዋርትን ጌታ ዳርንሌይን አገባች, እሱም የራሱን የእንግሊዝ ዙፋን ይዞ ነበር. ጋብቻው ድሉን ለስኮትላንድ ፕሮቴስታንቶች እና ለኤልዛቤት ካስረከበው በማርያም ከተከሰቱት ተከታታይ የፍርድ ስህተቶች የመጀመሪያው ነው። ዳርንሌይ በፍጥነት ተወዳጅነት አጥቷል እና በየካቲት 1567 በሴረኞች ተገደለ፣ በእርግጠኝነት በጄምስ ሄፕበርን ፣ 4ኛ አርል የ ። ብዙም ሳይቆይ፣ በሜይ 15፣ 1567፣ ሜሪ ቦዝዌልን አገባች፣ ይህም ባሏን በመግደል ላይ ተካፋይ እንደነበረች ጥርጣሬን አስነስቷል። ኤልሳቤጥ ማርያምን ስለ ጋብቻ ነገረቻት፣ እንዲህ በማለት ጻፈቻት። እንደዚህ አይነት ጉዳይ ለማግባት ከመቸኮል ይልቅ ለክብርሽ ከዚህ የከፋ ምርጫ እንዴት ሊደረግ ቻለ። እኛ በውሸት እናምናለን። እነዚህ ክስተቶች በሎክ ሌቨን ካስት ለማርያም ሽንፈት እና እስራት በፍጥነት አመሩ። የስኮትላንድ ጌቶች በሰኔ 1566 የተወለደውን ልጇን ጄምስ ስድስተኛን እንድትገልፅ አስገደዷት። ጄምስ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ሆኖ እንዲያድግ ወደ ስተርሊንግ ካስል ተወሰደ። ሜሪ በ1568 ከሎክ ሌቨን አመለጠች ነገርግን ሌላ ሽንፈት ካደረገች በኋላ ድንበሩን አቋርጣ ወደ እንግሊዝ ሸሸች። የኤልዛቤት የመጀመሪያዋ ደመ ነፍስ አብረዋት የነበሩትን ንጉሣዊቷን መመለስ ነበር; ግን እሷ እና ምክር ቤቷ በምትኩ በደህና መጫወትን መረጡ። ማርያምን ከእንግሊዝ ጦር ጋር ወደ ስኮትላንድ ከመመለስ ወይም ወደ ፈረንሣይና የእንግሊዝ ካቶሊካዊ ጠላቶች ከመላክ ይልቅ እንግሊዝ ውስጥ አስሯት ለቀጣዮቹ አሥራ ዘጠኝ ዓመታት ታስራለች። የካቶሊክ ምክንያት ማርያም ብዙም ሳይቆይ የአመፅ ትኩረት ሆነች። በ 1569 በሰሜን ውስጥ ትልቅ የካቶሊክ እምነት ተከታይ ነበር; ግቡ ማርያምን ነፃ ማውጣት፣ የኖርፎልክ 4ኛ መስፍን ከቶማስ ሃዋርድ ጋር ማግባት እና በእንግሊዝ ዙፋን ላይ ማስቀመጥ ነበር። አማፂዎቹ ከተሸነፉ በኋላ ከ750 በላይ የሚሆኑት በኤልዛቤት ትእዛዝ ተገድለዋል። ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፒዮስ አምስተኛ በ1570 ዓ.ም ረጅናንስ በኤክሴልሲስ የተሰኘ በሬ አወጡ፣ እሱም “ኤልዛቤት፣ የመሰለችው የእንግሊዝ ንግሥት እና የወንጀል አገልጋይ” እንድትገለል እና መናፍቅ እንደሆነች በማወጅ ሁሉንም ፈታለች። ለእሷ ከማንኛውም ታማኝነት ተገዢዎች ። ትእዛዞቿን የሚታዘዙ ካቶሊኮች የመገለል ዛቻ ደርሶባቸዋል። የጳጳሱ በሬ በፓርላማ በካቶሊኮች ላይ የሕግ አውጭ እርምጃዎችን ቀስቅሷል፣ ሆኖም ግን በኤልዛቤት ጣልቃ ገብነት የተቀነሰው። እ.ኤ.አ. በ 1581 የእንግሊዘኛ ትምህርቶችን ወደ ኤልዛቤት ያላቸውን ታማኝነት ለማንሳት "ዓላማ" ወደ ካቶሊካዊነት መለወጥ የሞት ቅጣትን የሚያስከትል ክህደት ፈፅሞ ነበር. ከ 1570 ዎቹ ጀምሮ ከአህጉራዊ ሴሚናሮች የተውጣጡ ሚስዮናውያን ካህናት በድብቅ ወደ እንግሊዝ ሄዱ "የእንግሊዝ ዳግመኛ መመለሻ" ምክንያት. ብዙዎች ተገድለዋል፣ የሰማዕትነት አምልኮን በመፍጠር። በኤክሴልሲስ የሚገኘው ሬጋንስ እንግሊዛዊ ካቶሊኮች ማርያምን እንደ ህጋዊ የእንግሊዝ ሉዓላዊ ገዢ እንድትመለከቱ ጠንካራ ማበረታቻ ሰጥቷቸዋል። ማርያም እሷን በእንግሊዝ ዙፋን ላይ ለማስቀመጥ ስለ እያንዳንዱ የካቶሊክ ሴራ አልተነገራቸውም ፣ ግን በ 1571 ከሪዶልፊ ሴራ (የማርያም ፈላጊ ፣ የኖርፎልክ መስፍን ፣ ጭንቅላቱን እንዲያጣ ያደረገው) በ 1586 ወደ ባቢንግተን ሴራ ፣ የኤልዛቤት የስለላ አስተዳዳሪ ሰር ፍራንሲስ ዋልሲንግሃም እና የንጉሣዊው ምክር ቤት በእሷ ላይ ክስ አሰባሰቡ። በመጀመሪያ ኤልሳቤጥ የማርያምን ሞት ጥሪ ተቃወመች። እ.ኤ.አ. በ 1586 መገባደጃ ላይ በባቢንግተን ሴራ ወቅት በተፃፉ ደብዳቤዎች ማስረጃ ላይ የማርያምን ችሎት እና ግድያ እንድትቀበል ተገፋፍታለች። የኤልዛቤት የቅጣት አዋጅ ማወጁ “የተነገረላት ማርያም፣ የአንድ ዘውድ ባለቤት መስሎ፣ በዛው ግዛት ውስጥ የተለያዩ ነገሮችን ዞራ በንጉሣዊው ሰውነታችን ላይ የሚደርሰውን ጉዳት፣ ሞት እና ጥፋት አስባ ነበር። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. ግድያው ከተፈጸመ በኋላ ኤልዛቤት የተፈረመውን የግድያ ማዘዣ እንዲላክ አላሰበችም ስትል ፀሐፊዋን ዊልያም ዴቪሰንን ሳታውቅ ተግባራዊ አድርጋለች በማለት ወቅሳለች። የኤልዛቤት ፀፀት ቅንነት እና የፍርድ ቤት ማዘዣውን ለማዘግየት ፈለገች ወይስ አልፈለገችም በዘመኗም ሆነ በኋላ የታሪክ ፀሃፊዎች ጥያቄ ውስጥ ገብተዋል። ጦርነቶች እና የባህር ማዶ ንግድ የኤልዛቤት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በአብዛኛው መከላከያ ነበር። ለየት ያለ ሁኔታ ከጥቅምት 1562 እስከ ሰኔ 1563 ድረስ የእንግሊዝ የሌሃቭር ይዞታ ነበር፣ ይህ የሆነው የኤልዛቤት ሁጉኖት አጋሮች ከካቶሊኮች ጋር በመተባበር ወደቡን መልሶ ለመያዝ ባደረገ ጊዜ ሳይሳካ ቀርቷል። የኤልዛቤት አላማ በጥር 1558 በፈረንሣይ የተሸነፈችውን ሌሃቭርን ወደ ካሌ መቀየር ነበር። ይህ ከስፔን ጋር በተደረገው ጦርነት ፍሬያማ የሆነ ሲሆን 80 በመቶው የተካሄደው በባህር ላይ ነው። እ.ኤ.አ. ከ1577 እስከ 1580 ድረስ ፍራንሲስ ድሬክን ከዞረ በኋላ ፈረሰች እና በስፔን ወደቦች እና መርከቦች ላይ ባደረገው ወረራ ታዋቂነትን አገኘ። የባህር ላይ ዝርፊያ እና ራስን ማበልጸግ ንግሥቲቱ ብዙም ቁጥጥር ያልነበራቸው የኤሊዛቤት የባህር ተጓዦችን አባረራቸው። በ1562-1563 ሌሃቭር ከተያዘች እና ከጠፋች በኋላ ኤልዛቤት እስከ 1585 ድረስ የእንግሊዝ ጦር በላከችበት ወቅት በአህጉሪቱ ወታደራዊ ጉዞዎችን ከማድረግ ተቆጥባ የፕሮቴስታንት ደች ሆላንድን በፊሊፕ ላይ ያመፀው ።ይህም በ 1584 የንግስቲቱ አጋሮች ዊልያም ሞትን ተከትሎ ነበር ። ዝምተኛው፣ የብርቱካን ልዑል፣ እና የአንጁው መስፍን፣ እና ተከታታይ የደች ከተማዎች ለስፔን ኔዘርላንድስ የፊልጶስ ገዥ የፓርማ መስፍን አሌክሳንደር ፋርኔስ መሰጠታቸው። በታህሳስ 1584 በፊሊፕ እና በፈረንሣይ ካቶሊካዊ ሊግ በጆይንቪል መካከል የተደረገ ጥምረት የአንጁ ወንድም ፈረንሣዊው ሄንሪ ሳልሳዊ የስፔን የኔዘርላንድን የበላይነት ለመቃወም ያለውን አቅም አሳጣው። በተጨማሪም የካቶሊክ ሊግ ጠንካራ በሆነበት በፈረንሳይ የባህር ዳርቻ ላይ የስፓኒሽ ተጽእኖን አስፋፍቷል እና እንግሊዝን ለወረራ አጋልጧል። እ.ኤ.አ. በ1585 የበጋው ወቅት አንትወርፕ የፓርማ መስፍን ከበባ በእንግሊዘኛ እና በ ደች. ውጤቱም ኤልዛቤት ለደች ወታደራዊ ድጋፍ ለመስጠት ቃል የገባችበት የነሀሴ 1585 የኖንሱች ስምምነት ነበር። ስምምነቱ እ.ኤ.አ. በ 1604 እስከ ለንደን ስምምነት ድረስ የዘለቀውን የአንግሎ-ስፓኒሽ ጦርነት መጀመሪያ ያመላክታል ። ጉዞውን የተመራው በኤልዛቤት የቀድሞ ፈላጊ፣ የሌስተር አርል ነው። ኤልዛቤት ከጅምሩ ይህን ተግባር አልደገፈችም። ሌስተር ሆላንድ በገባ በቀናት ውስጥ ከስፔን ጋር ሚስጥራዊ የሰላም ድርድር ስትጀምር ላዩን ላይ ያሉትን ደች በእንግሊዝ ጦር ለመደገፍ የነበራት ስልቷ ከሌስተር ጋር ግጭት ውስጥ መግባት ነበረበት። ንቁ ዘመቻ. ኤልዛቤት በበኩሏ "ከጠላት ጋር ምንም አይነት ወሳኝ እርምጃ እንዳይወስድ" ትፈልጋለች። ከኔዘርላንድስ ጄኔራል የጠቅላይ ገዥነት ቦታ በመቀበል ኤልዛቤትን አስቆጣች። ኤልዛቤት ይህንን የኔዘርላንድስ ሉዓላዊነት እንድትቀበል ለማስገደድ የተደረገ የደች ተንኮል አድርጋ ተመለከተች፣ይህም እስካሁን ድረስ ሁሌም ውድቅ አድርጋ ነበር። ለሌስተር ጻፈች፡- ከዚች ምድር ርዕሰ ጉዳይ በላይ የሆነ ሰው በራሳችን ተነሥቶ በእኛ እጅግ የተወደደ፣ በንቀት ምክንያት ትእዛዛችንን ይጥሳል ብለን ልንገምት አንችልም ነበር (በልምምድ ሲወድቅ ባናውቅ ኖሮ)። በአክብሮት እጅግ በጣም የሚነካን ... እና ስለዚህ የእኛ ግልጽ ደስታ እና ትዕዛዛት ፣ ሁሉም መዘግየቶች እና ማመካኛዎች ተለያይተው ፣ በታማኝነትዎ ግዴታ ላይ ወዲያውኑ ታዘዙ እና የዚህ ተሸካሚው በእኛ ውስጥ እንዲያደርጉ የሚዘዙትን ሁሉ እንዲፈጽሙ ነው። ስም ስለዚህም አትሳቱ፣ በተቻለ መጠን ተቃራኒውን መልስ እንደምትሰጥ። የኤልዛቤት “ትዕዛዝ” መልእክተኛዋ የተቃውሞ ደብዳቤዋን በሆላንድ ምክር ቤት ፊት በይፋ በማንበብ ሌስተር በአቅራቢያው መቆም ነበረባት። ይህ የ"ሌተናል ጄኔራል" ህዝባዊ ውርደት ከስፔን ጋር የተለየ ሰላም ለመፍጠር ከቀጠለችበት ንግግር ጋር ተዳምሮ ሌስተር በኔዘርላንድስ መካከል ያለውን አቋም በማያዳግም ሁኔታ አሳፈረ። ኤልዛቤት በረሃብ ለተቸገሩ ወታደሮቿ ቃል የተገባለትን ገንዘብ ለመላክ ደጋግማ በመቅረቷ ወታደራዊ ዘመቻው ክፉኛ ተስተጓጎለ። ለጉዳዩ እራሷን ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆኗ፣ እንደ ፖለቲካ እና ወታደራዊ መሪ የሌስተር ድክመቷ፣ እና በቡድን የተሞላው እና የተመሰቃቀለው የኔዘርላንድ ፖለቲካ ሁኔታ የዘመቻውን ውድቀት አስከትሏል። በመጨረሻም ሌስተር ትእዛዙን በታህሳስ 1587 ለቀቀ። የስፔን አርማዳ ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ሰር ፍራንሲስ ድሬክ በ1585 እና በ1586 በካሪቢያን ባህር በሚገኙ የስፔን ወደቦች እና መርከቦች ላይ ትልቅ ጉዞ አድርጓል። ጦርነቱን ወደ እንግሊዝ ለመውሰድ ወስኗል ። እ.ኤ.አ. ሐምሌ 12 ቀን 1588 የስፔን አርማዳ ፣ ታላቅ የመርከብ መርከቦች ፣ የስፔን ወረራ ኃይልን በፓርማ መስፍን ስር ከኔዘርላንድ ወደ ደቡብ ምስራቅ እንግሊዝ የባህር ዳርቻ ለማጓጓዝ በማቀድ ወደ ጣቢያው ተጓዙ ። የስፔን መርከቦችን ወደ ሰሜናዊ ምስራቅ የበተነው የተሳሳተ ስሌት፣ መጥፎ ዕድል እና የእንግሊዝ የእሳት አደጋ መርከቦች በጁላይ 29 ከግሬቪላይን ላይ የተደረገ ጥቃት፣ አርማዳውን አሸንፏል። የአየርላንድ የባህር ዳርቻ (አንዳንድ መርከቦች በሰሜን ባህር በኩል ወደ ስፔን ለመመለስ ከሞከሩ በኋላ እና በአየርላንድ ምዕራባዊ የባህር ጠረፍ በኩል ወደ ደቡብ ይመለሱ)። የአርማዳውን እጣ ፈንታ ሳያውቁ የእንግሊዝ ሚሊሻዎች በሌስተር ኦፍ ሌስተር ትእዛዝ ሀገሪቱን ለመከላከል ተሰበሰቡ። ሌስተር ኤልዛቤት ወታደሮቿን በኤሴክስ በቲልበሪ እንድትመረምር ነሐሴ 8 ጋብዟታል። በነጭ ቬልቬት ቀሚስ ላይ የብር ጡት ለብሳ በጣም ዝነኛ በሆነው ንግግሯ ላይ እንዲህ ብላ ተናግራቸዋለች። አፍቃሪ ወገኖቼ፣ ለደህንነታችን በሚጠነቀቁ አንዳንድ ሰዎች አሳምነናል፣ ክህደትን በመፍራት ራሳችንን ለታጠቁ ሰዎች እንዴት እንደምንሰጥ እንጠንቀቅ። ነገር ግን እውነት እላችኋለሁ፥ ታማኝና አፍቃሪ ሕዝቤን ሳልታመን ልኖር አልወድም... ደካማና ደካማ ሴት አካል እንዳለኝ አውቃለሁ፥ ነገር ግን የንጉሥና የንጉሥ ልብና ሆድ አለኝ። የእንግሊዝ አገር፣ እና ፓርማ ወይም ስፔን፣ ወይም ማንኛውም የአውሮፓ ልዑል የግዛቴን ድንበሮች ሊደፍሩ ይገባል ብለው መጥፎ ንቀት ያስቡ።ወረራ ሳይመጣ ህዝቡ ተደሰተ። በቅዱስ ጳውሎስ ካቴድራል ለምስጋና አገልግሎት የኤልሳቤጥ ሰልፍ የዘውድ ንግዷን እንደ ትርኢት ተቀናቃኙ። የአርማዳ ሽንፈት ለኤልዛቤትም ሆነ ለፕሮቴስታንት እንግሊዝ ጠንካራ የፕሮፓጋንዳ ድል ነበር። እንግሊዛውያን በድንግል ንግሥት ሥር የእግዚአብሔርን ሞገስ እና ሀገሪቱን የማይደፈርስ ምልክት አድርገው ይወስዱታል። ይሁን እንጂ ድሉ በጦርነቱ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ማምጣት አልቻለም, ይህም ቀጥሏል እና ብዙ ጊዜ ለስፔን ይጠቅማል. ስፔናውያን የኔዘርላንድን ደቡባዊ ግዛቶች አሁንም ይቆጣጠሩ ነበር, እናም የወረራ ስጋት አሁንም አለ. ሰር ዋልተር ራሌይ ከሞተች በኋላ የኤልዛቤት ማስጠንቀቂያ ከስፔን ጋር የሚደረገውን ጦርነት እንዳደናቀፈ ተናግሯል፡- ሟች ንግሥት እንደ ጸሐፍዎቿ ሁሉ ተዋጊዎቿን ብታምን ኖሮ፣ እኛ በሷ ጊዜ ያን ታላቅ ግዛት ጨፍጭፈን ንጉሣቸውን በሾላና በብርቱካን አደረግን እንደ ቀድሞው ዘመን። ነገር ግን ግርማዊነቷ ሁሉንም ነገር በግማሽ ያደረጉ ሲሆን በጥቃቅን ወረራዎች ስፔናዊውን እራሱን እንዴት መከላከል እንዳለበት እና የራሱን ድክመት እንዲያይ አስተምሮታል። ምንም እንኳን አንዳንድ የታሪክ ምሁራን ኤልዛቤትን በተመሳሳይ ምክንያቶች ቢተቹም፣ የራሌይ ብይን ብዙ ጊዜ ኢ-ፍትሃዊ ነው ተብሏል። ኤልዛቤት እራሷ እንዳስቀመጠችው በአንድ ወቅት በተግባር ባሳዩት አዛዦቿ ላይ ብዙ እምነት እንዳትጥል በቂ ምክንያት ነበራት። እ.ኤ.አ. በ1589፣ ከስፔን አርማዳ በኋላ፣ ኤልዛቤት የእንግሊዙን አርማዳ ወይም ከ23,375 ሰዎች እና 150 መርከቦች ጋር፣ በሰር ፍራንሲስ ድራክ እንደ አድሚራል እና ሰር ጆን ኖሬይስ በጄኔራልነት ወደ ስፔን ላከች። የእንግሊዝ መርከቦች ከ11,000–15,000 ሰዎች ተገድለዋል፣ ቆስለዋል ወይም በበሽታ ሞቱ እና 40 መርከቦች በመስጠም ወይም በመማረክ አስከፊ ሽንፈት ደርሶባቸዋል። እንግሊዝ በስፔን አርማዳ ላይ ያሸነፈችው ጥቅም ጠፋ፣ እና የስፔን ድል በሚቀጥሉት አስርት አመታት ውስጥ የፊሊፕ 2ኛ የባህር ሃይል መነቃቃትን አሳይቷል። በ 1589 የፕሮቴስታንት ሄንሪ አራተኛ የፈረንሳይን ዙፋን ሲወርስ, ኤልዛቤት ወታደራዊ ድጋፍ ላከችው. በ1563 ከሌ ሃቭር ካፈገፈገች በኋላ ወደ ፈረንሳይ የመግባት የመጀመሪያዋ የመጀመሪያዋ ነበር።የሄንሪ ርስት በካቶሊክ ሊግ እና በፊሊፕ 2ኛ ከፍተኛ ክርክር ነበረበት።እና ኤልዛቤት የስፔን የቻናል ወደቦችን እንዳይቆጣጠር ፈራች። በፈረንሳይ ተከታዩ የእንግሊዝኛ ዘመቻዎች ግን ያልተደራጁ እና ውጤታማ አልነበሩም። ፔሬግሪን በርቲ፣ 13ኛ ባሮን ዊሎቢ ደ ኤሬስቢ፣ በአብዛኛው የኤልዛቤትን ትእዛዝ ችላ በማለት፣ በሰሜን ፈረንሳይ ብዙም ሳይቆይ 4,000 ሰራዊት ይዞ ዞረ። በታህሳስ 1589 ግማሹን ወታደሮቹን በማጣቱ በችግር ውስጥ ወድቋል። በ1591፣ 3,000 ሰዎችን ወደ ብሪታኒ የመራው የጆን ኖሬይስ ዘመቻ የበለጠ ጥፋት ነበር። እንደነዚህ ያሉትን ጉዞዎች በተመለከተ፣ ኤልዛቤት አዛዦቹ በጠየቁት አቅርቦቶች እና ማጠናከሪያዎች ላይ ኢንቨስት ለማድረግ ፈቃደኛ አልነበራትም። ኖርሬስ ለበለጠ ድጋፍ በአካል ለመማፀን ወደ ለንደን ሄደ። እሱ በሌለበት ጊዜ፣ አንድ የካቶሊክ ሊግ ጦር በግንቦት 1591 በሰሜን ምዕራብ ፈረንሳይ ክራኦን የሠራዊቱን አጽም ለማጥፋት ተቃርቧል። በሐምሌ ወር ኤልዛቤት ሄንሪ አራተኛን እንዲከበብ ለመርዳት በሮበርት ዴቬሬክስ፣ የኤሴክስ 2ኛ አርል የሚመራ ሌላ ጦር ላከች። ሩዋን ውጤቱም እንዲሁ አስከፊ ነበር። ኤሴክስ ምንም ነገር አላደረገም እና በጥር 1592 ወደ ቤት ተመለሰ። ሄንሪ በሚያዝያ ወር ከበባውን ተወ። እንደተለመደው ኤልዛቤት ከአዛዦቿ ውጭ አገር ከነበሩ በኋላ መቆጣጠር አልቻለችም። ስለ ኤሴክስ “እሱ ባለበት፣ ወይም የሚያደርገው፣ ወይም ምን ማድረግ እንዳለበት፣ እኛ አላዋቂዎች ነን” ስትል ጽፋለች። አየርላንድ ከሁለቱ መንግሥቶቿ አንዷ ብትሆንም፣ ኤልዛቤት በጠላትነት ፈርጆ ነበር፣ እና በራስ ገዝ በምትሆን ቦታ፣ የአየርላንድ ሕዝብ የካቶሊክ እምነት ተከታይ የሆነች እና ሥልጣኗን ለመቃወም እና ከጠላቶቿ ጋር ለማሴር ፈቃደኛ ነበረች። በዚያ የነበራት ፖሊሲ ለአሽከሮችዎቿን መሬት መስጠት እና አማፂያኑ ስፔንን እንግሊዝን የምታጠቁበት መሰረት እንዳይሰጡ ማድረግ ነበር። በተከታታይ ህዝባዊ አመጽ የዘውዱ ሃይሎች መሬቱን በማቃጠል ወንድ፣ ሴትና ህጻን ጨፍጭፈዋል። እ.ኤ.አ. ገጣሚው እና ቅኝ ገጣሚው ኤድመንድ ስፔንሰር ተጎጂዎቹ "ማንኛውም የድንጋይ ልብ እንዲሁ ያበላሸው ነበር" ሲል ጽፏል። ኤልዛቤት አዛዦቿን አይሪሽ፣ “ያ ጨዋና አረመኔያዊ ሕዝብ” በደንብ እንዲያዙ መከረቻቸው። ነገር ግን እሷ ወይም አዛዦቿ ኃይል እና ደም መፋሰስ ፈላጭ ቆራጭ አላማቸውን ሲፈጽሙ ምንም አይነት ጸጸት አላሳዩም። እ.ኤ.አ. በ 1594 እና 1603 መካከል ፣ ኤልዛቤት በአየርላንድ በዘጠኝ ዓመታት ጦርነት ወቅት እጅግ በጣም ከባድ ፈተና ገጠማት ፣ ከስፔን ጋር በተደረገው ከፍተኛ ጦርነት ፣ የአመፅ መሪውን ሂዩ ኦኔል ፣ የታይሮናዊውን አርል ደግፋለች። በ 1599 ጸደይ, ኤልዛቤት አመፁን ለማጥፋት ሮበርት ዴቬሬክስ, 2 ኛ አርል ኦቭ ኤሴክስ ላከ. ለብስጭቷ፣ ትንሽ እድገት አላደረገም እና ትእዛዟን በመጣስ ወደ እንግሊዝ ተመለሰ። እሱ በቻርልስ ብሎንት ተተካ፣ ሎርድ ሞንጆይ፣ አመጸኞቹን ለማሸነፍ ሦስት ዓመታት ፈጅቷል። ኦኔል በመጨረሻ ኤልዛቤት ከሞተች ከጥቂት ቀናት በኋላ በ1603 እጁን ሰጠ። ብዙም ሳይቆይ በእንግሊዝ እና በስፔን መካከል የሰላም ስምምነት ተፈረመ። ኤልዛቤት በመጀመሪያ በግማሽ ወንድሟ በኤድዋርድ ስድስተኛ የተቋቋመውን ከሩሲያው ጋር ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቀጠለች ። ብዙ ጊዜ ለኢቫን ዘሪብል በትህትና ትጽፍ ነበር፣ ምንም እንኳን ዛር ብዙ ጊዜ በወታደራዊ ህብረት ላይ ከማተኮር ይልቅ በንግድ ላይ ባላት ትኩረት ተበሳጭታ ነበር። ዛር እንኳን አንድ ጊዜ ሀሳብ አቀረበላት እና በኋለኛው የግዛት ዘመን ግዛቱ አደጋ ላይ ከወደቀ በእንግሊዝ ጥገኝነት እንዲሰጥ ዋስትና ጠየቀ።የሙስኮቪ ኩባንያ ተወካይ ሆኖ ስራውን የጀመረው እንግሊዛዊው ነጋዴ እና አሳሽ አንቶኒ ጄንኪንሰን ሆነ። በኢቫን ዘሪብል ፍርድ ቤት የንግሥቲቱ ልዩ አምባሳደር በ1584 ኢቫን ሲሞት፣ ብዙም ፍላጎት የሌለው ልጁ ፌዮዶር ተተካ። እንደ አባቱ ሳይሆን ፌዮዶር ከእንግሊዝ ጋር ልዩ የንግድ መብቶችን ለማስጠበቅ ምንም ቅንዓት አልነበረውም። ፌዮዶር መንግስቱን ለሁሉም የውጭ ዜጎች ክፍት መሆኑን አውጇል እና ኢቫን በቸልታ የታገሉትን የእንግሊዝ አምባሳደር ሰር ጀሮም ቦውስን አሰናበተ። ኤልዛቤት አዲስ አምባሳደርን ዶክተር ጊልስ ፍሌቸርን ላከች ከገዢው ቦሪስ ጎዱኖቭ ዛርን እንደገና እንዲያጤነው እንዲያሳምንለት ለመጠየቅ። ድርድሩ ከሽፏል፣ ፍሌቸር ፌዮዶርን ከበርካታ ርዕሶች ሁለቱን በማውጣቱ ምክንያት። ኤልዛቤት በግማሽ ማራኪ፣ ግማሽ የሚያንቋሽሽ ደብዳቤዎች ለፌዮዶር ይግባኝ ማለቷን ቀጠለች። ኅብረት እንዲመሠርት ሐሳብ አቀረበች፣ ከፌዮዶር አባት ሲቀርብላት ለማድረግ ፈቃደኛ ያልሆነችውን ነገር ግን ውድቅ ተደረገች። የሙስሊም ግዛቶች በኤልዛቤት የግዛት ዘመን በእንግሊዝ እና በባርበሪ ግዛቶች መካከል የንግድ እና የዲፕሎማሲ ግንኙነት ተፈጠረ። እንግሊዝ ከስፔን ጋር በመቃወም ከሞሮኮ ጋር የንግድ ግንኙነት መስርታ የጦር ትጥቅ፣ ጥይቶች፣ እንጨትና ብረት በመሸጥ የሞሮኮ ስኳር በመሸጥ ላይ ነበር፣ ምንም እንኳን የፓፓል እገዳ ቢኖርበትም። በ1600 የሞሮኮ ገዥ ሙላይ አህመድ አል ማንሱር ዋና ፀሀፊ አብዱል ኦዋህድ ቤን መስኡድ በንግሥት ኤልሳቤጥ ቀዳማዊ ፍርድ ቤት አምባሳደር በመሆን እንግሊዝን ጎበኘ፣ የአንግሎ-ሞሮኮ ኅብረትን በስፔን ላይ ለመደራደር። ኤልዛቤት “ተስማማች። የጦር መሳሪያ ቁሳቁሶችን ለሞሮኮ ለመሸጥ እና እሷ እና ሙላይ አህመድ አል-ማንሱር በስፔን ላይ የጋራ ዘመቻ ስለመጀመር ተነጋገሩ። ይሁን እንጂ ውይይቶቹ ያልተቋረጡ ሲሆን ሁለቱም ገዥዎች ከኤምባሲው በሁለት ዓመታት ውስጥ ሞተዋል. ከኦቶማን ኢምፓየር ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትም በሌቫንት ካምፓኒ ቻርተር እና የመጀመሪያውን የእንግሊዝ አምባሳደር ወደ ፖርቴ በመላክ በ1578 ዓ.ም. በሁለቱም አቅጣጫዎች ተልከዋል እና በኤሊዛቤት እና በሱልጣን ሙራድ መካከል የኤፒስቶላር ልውውጥ ተደረገ። በአንድ የደብዳቤ ልውውጡ ላይ፣ ሙራድ እስልምና እና ፕሮቴስታንት “ከሮማ ካቶሊክ ጋር ካደረጉት የበለጠ የሚያመሳስላቸው ነገር አለ፣ ሁለቱም የጣዖት አምልኮን አይቀበሉም” የሚለውን አስተሳሰብ አስተናግዶ በእንግሊዝ እና በኦቶማን ኢምፓየር መካከል ህብረት ለመፍጠር ተከራክሯል። ካቶሊካዊ አውሮፓ፣ እንግሊዝ ቆርቆሮ እና እርሳስ (ለመድፍ ለመወርወር) እና ጥይቶችን ወደ ኦቶማን ኢምፓየር ላከች እና ኤልዛቤት በ1585 ከስፔን ጋር ጦርነት በተቀሰቀሰበት ወቅት ፍራንሲስ ዋልሲንግሃም በቀጥታ ኦቶማን እንዲመራ ሲጠይቅ ከሙራድ ጋር በጋራ ወታደራዊ ዘመቻ ላይ በቁም ነገር ተወያይታለች። የጋራ የስፔን ጠላት ላይ ወታደራዊ ተሳትፎ በ1583፣ ሰር ሃምፍሬይ ጊልበርት በኒውፋውንድላንድ ላይ ቅኝ ግዛት ለመመስረት ወደ ምዕራብ ተጓዙ። ወደ እንግሊዝ አልተመለሰም። የጊልበርት ዘመድ ሰር ዋልተር ራሌይ የአትላንቲክ ውቅያኖስን ቃኝተው የቨርጂኒያ ግዛት ይገባኛል፣ ምናልባት ለኤልዛቤት፣ “ድንግል ንግሥት” ክብር የተሰየመ ሊሆን ይችላል። ይህ ግዛት ከኒው ኢንግላንድ እስከ ካሮላይና ድረስ ካለው ከአሁኑ የቨርጂኒያ ግዛት በጣም ትልቅ ነበር። በ1585 ራሌይ ከጥቂት ሰዎች ጋር ወደ ቨርጂኒያ ተመለሰ። ከአሁኑ ሰሜን ካሮላይና ወጣ ብላ በምትገኘው በሮአኖክ ደሴት አረፉ። ከመጀመሪያው ቅኝ ግዛት ውድቀት በኋላ ራሌይ ሌላ ቡድን መለመለ እና ጆን ዋይትን አዛዥ አደረገው። ራሌይ በ1590 ሲመለስ የተወው የሮአኖክ ቅኝ ግዛት ምንም ዱካ አልተገኘም ነገር ግን በሰሜን አሜሪካ የመጀመሪያው የእንግሊዝ ሰፈራ ነበር። የምስራቅ ህንድ ኩባንያ የምስራቅ ህንድ ኩባንያ በህንድ ውቅያኖስ ክልል እና በቻይና ለመገበያየት የተቋቋመ ሲሆን በታህሳስ 31 ቀን 1600 ቻርተሩን ከንግሥት ኤልዛቤት ተቀበለ ። ለ 15 ዓመታት ኩባንያው በምስራቅ ምስራቅ ካሉ አገሮች ጋር በእንግሊዝ ንግድ ላይ በሞኖፖል ተሸልሟል ። የጥሩ ተስፋ ኬፕ እና የማጅላን የባህር ዳርቻዎች ምዕራብ። ሰር ጀምስ ላንካስተር በ1601 የመጀመሪያውን ጉዞ አዘዙ። ኩባንያው በ18ኛው እና በ19ኛው ክፍለ ዘመን በህንድ ውስጥ ግማሹን የአለም ንግድ እና ጠቃሚ ግዛት ተቆጣጠረ። የግርማዊቷ ንግስና መጨረሻ መምጣት እ.ኤ.አ. በ 1588 የስፔን አርማዳ ከተሸነፈ በኋላ ያለው ጊዜ ለኤልዛቤት እስከ ንግሥናዋ መጨረሻ ድረስ አዲስ ችግሮች አምጥቷል ። ከስፔን እና አየርላንድ ጋር የነበረው ግጭት እየገፋ ሲሄድ የግብር ሸክሙ እየከበደ ሄዶ ኢኮኖሚው ደካማ በሆነ ምርት ተመታ። የጦርነት ዋጋ. ዋጋ ጨምሯል እና የኑሮ ደረጃው ቀንሷል። በዚህ ጊዜ የካቶሊኮች ጭቆና ተባብሷል እና ኤልዛቤት በ1591 የካቶሊክን ሰዎች እንዲጠይቁ እና እንዲከታተሉ ኮሚሽኖችን ሰጠች። የሰላም እና የብልጽግናን ቅዠት ለማስቀጠል በውስጣዊ ሰላዮች እና ፕሮፓጋንዳ ላይ ትተማመናለች። በመጨረሻዎቹ ዓመታት ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣ ትችት ህዝቡ ለእሷ ያለው ፍቅር ማሽቆልቆሉን ያሳያል።ለዚህ “ሁለተኛው የግዛት ዘመን” የኤልዛቤት አንዱ መንስኤ፣ አንዳንድ ጊዜ ተብሎ እንደሚጠራው፣ በ1590ዎቹ ውስጥ የነበረው የግላዊነት ምክር ቤት የኤልዛቤት አስተዳደር አካል የተለወጠ ባህሪ ነው። አዲስ ትውልድ በስልጣን ላይ ነበር። ከሎርድ በርግሌይ በስተቀር፣ በ1590 አካባቢ በጣም አስፈላጊዎቹ ፖለቲከኞች ሞተዋል፡ የሌስተር አርል በ1588 ዓ.ም. ሰር ፍራንሲስ ዋልሲንግሃም በ1590 ዓ.ም. እና ሰር ክሪስቶፈር ሃቶን በ1591። ከ1590ዎቹ በፊት በመንግስት ውስጥ ከፋፋይ ግጭትና ግጭት አሁን መለያው ሆነ በሎርድ በርግሌይ ልጅ በሮበርት ሴሲል እና በሎርድ ቡርግሌይ ልጅ መካከል መራራ ፉክክር ተፈጠረ። እና በግዛቱ ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን ለመያዝ የተደረገው ትግል ፖለቲካውን አበላሽቷል። በ1594 ታማኝ በሆነው ዶክተር ሎፔዝ ጉዳይ ላይ እንደሚታየው የንግሥቲቱ የግል ሥልጣን እየቀነሰ ነበር። በኤርል ኦፍ ኤሴክስ በአገር ክህደት በስህተት በተከሰሰበት ወቅት፣ በመታሰሩ የተናደደች እና ጥፋቱን ያላመነች ቢመስልም ከመገደሉ ማስቀረት አልቻለችም። በመጨረሻዎቹ የንግሥና ዓመታት ኤልዛቤት በጦርነት ጊዜ ተጨማሪ ድጎማዎችን ለፓርላማ ከመጠየቅ ይልቅ ሞኖፖሊዎችን ከዋጋ ነፃ የሆነ የደጋፊነት ስርዓት በመስጠቱ ላይ ትተማመን ነበር። በሕዝብ ወጪ የቤተ መንግሥት አባላትን ማበልጸግ እና ቂም መብዛት። ይህ በ 1601 ፓርላማ ውስጥ በኮመንስ ሃውስ ውስጥ ቅስቀሳ አብቅቷል ። እ.ኤ.አ. ህዳር 30 ቀን 1601 በታዋቂው “ወርቃማው ንግግር” በኋይትሆል ቤተመንግስት 140 አባላትን ለተወካዩት ኤልዛቤት በደሉን እንደማታውቅ ተናግራ አባላቱን በተስፋ ቃል አሸንፋለች። እና ለስሜቶች የተለመደው ይግባኝሉዓላዊነታቸውን ከስህተቱ ሂደት የሚጠብቃቸው፣ በድንቁርና ሳይሆን በዐላማ ወድቀው ሊሆን ይችላል፣ ምን ምስጋና ይገባቸዋል፣ ቢገምቱትም እናውቃለን። እናም የዜጎቻችንን ልብ በፍቅር ከመጠበቅ የበለጠ ውድ ነገር ስላልሆነ፣ የነጻነታችንን ተሳዳቢዎች፣ የህዝባችን አራማጆች፣ የድሆች ጠላፊዎች ባይነገሩን ኖሮ ምንኛ ያልተገባ ጥርጣሬ ፈጠርን ነበር። !በኢኮኖሚና በፖለቲካዊ አለመረጋጋት የታየበት ተመሳሳይ ወቅት ግን በእንግሊዝ ታይቶ የማይታወቅ የስነ-ጽሁፍ አበባ አፍርቷል። በ1578 ከጆን ሊሊ ኢፉዌስ እና ከኤድመንድ ስፔንሰር ዘ ሼፐርድስ ካላንደር ጋር በ1578 ዓ.ም. በ1590ዎቹ የእንግሊዝ ሥነ-ጽሑፍ ታዋቂ የሆኑ አንዳንድ ታዋቂዎች በኤልዛቤት የግዛት ዘመን በሁለተኛው አስርት ዓመታት መጨረሻ ላይ የአዲሱ ሥነ-ጽሑፍ እንቅስቃሴ የመጀመሪያ ምልክቶች ታይተዋል። ዊልያም ሼክስፒር እና ክሪስቶፈር ማርሎዌን ጨምሮ። በያቆብ ዘመን በመቀጠል፣ የእንግሊዝ ቲያትር ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይደርሳል።የታላቅ የኤልዛቤት ዘመን አስተሳሰብ በአብዛኛው የተመካው በኤልሳቤጥ የግዛት ዘመን ንቁ ተሳትፎ በነበሩት ግንበኞች፣ ድራማ ባለሙያዎች፣ ገጣሚዎች እና ሙዚቀኞች ላይ ነው። የኪነ ጥበብ ዋና ደጋፊ ላልሆነችው ንግሥቲቱ በቀጥታ የተበደሩት ትንሽ ነው። ኤልዛቤት ሲያረጅ ምስሏ ቀስ በቀስ ተለወጠ። እሷ እንደ ቤልፎቤ ወይም አስትሪያ፣ እና ከአርማዳ በኋላ፣ እንደ ግሎሪያና፣ የኤድመንድ ስፔንሰር ግጥም ዘላለማዊ ወጣት ፌሪ ኩዊን ተመሰለች። ኤልዛቤት ለኤድመንድ ስፔንሰር የጡረታ አበል ሰጠች; ይህ ለእሷ ያልተለመደ ስለነበር ሥራውን እንደወደደች ያሳያል። የተሳሉት የቁም ሥዕሎቿ ከእውነታው የራቁ ሆኑ እና ከእርሷ በጣም እንድታንስ ያደረጓት የእንቆቅልሽ አዶዎች ስብስብ ሆኑ። እንዲያውም ቆዳዋ በ1562 በፈንጣጣ ተጎድቶ ነበር፣ ግማሹ ራሰ በራዋን ትቶ በዊግ እና በመዋቢያዎች ላይ ጥገኛ ነች። ጣፋጮች መውደዷ እና የጥርስ ሀኪሞችን መፍራት ለከባድ የጥርስ መበስበስ እና ኪሳራ አስተዋጽኦ አድርጓል በዚህም መጠን የውጪ ሀገራት አምባሳደሮች ንግግሯን ለመረዳት እስኪቸገሩ ድረስ የፈረንሳዩ ሄንሪ አራተኛ ልዩ አምባሳደር አንድሬ ሁራልት ደ ማይሴ ከንግስቲቱ ጋር ተገኝተው ነበር ። በዚህ ጊዜ "ጥርሶቿ በጣም ቢጫ እና እኩል አይደሉም ... በግራ በኩል ደግሞ ከቀኝ ያነሱ ናቸው. ብዙዎቹ ጠፍተዋል, ስለዚህም በፍጥነት ስትናገር ሰው በቀላሉ ሊረዳት አይችልም." እሱ ግን አክሎም፣ “መልክዋ ፍትሃዊ እና ረጅም እና በምታደርገው ነገር ሁሉ የተዋበች ናት፤ እስከሆነ ድረስ ክብሯን ትጠብቃለች፣ ነገር ግን በትህትና እና በጸጋ። ሰር ዋልተር ራሌይ "ጊዜ ያስገረማት ሴት" ብሏታል።የኤልዛቤት ውበቷ እየደበዘዘ በሄደ ቁጥር አሽከሮችዎቿ ያወድሱታል። ኤልዛቤት ይህን ሚና በመጫወት ደስተኛ ነበረች፣ነገር ግን በህይወቷ የመጨረሻ አስር አመታት ውስጥ የራሷን አፈጻጸም ማመን ጀምራለች። የሌስተር የእንጀራ ልጅ የሆነችውን እና እሷን ይቅር ያለችለትን የማራኪውን ወጣት ሮበርት ዴቬሬክስን፣ አርል ኦቭ ኤሴክስን ትወዳለች እና ትወደዋለች። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሚሄደው ኃላፊነት የጎደለው ድርጊት ቢሆንም፣ እሷም ለወታደርነት ሾመችው። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በየካቲት 1601 ጆርጅ በለንደን አመጽ ለማነሳሳት ሞከረ። ንግሥቲቱን ሊይዝ አስቦ ነበር ነገር ግን ጥቂቶች ለድጋፉ ተሰበሰቡ እና በየካቲት 25 አንገቱ ተቆርጧል። ኤልዛቤት ለዚህ ክስተት በከፊል ተጠያቂው የራሷ የተሳሳተ ፍርድ እንደሆነ ታውቃለች። አንድ ታዛቢ በ1602 እንዲህ ሲል ጽፏል:- “ደስታዋ በጨለማ ውስጥ መቀመጥ እና አንዳንድ ጊዜ እንባ በማፍሰስ ኤሴክስን ለማልቀስ ነው። የኤልዛቤት ከፍተኛ አማካሪ ዊልያም ሴሲል 1ኛ ባሮን በርግሌይ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 4 ቀን 1598 ሞተ። የፖለቲካ ካባው ለልጁ ሮበርት ሴሲል ተላለፈ፣ እሱም ብዙም ሳይቆይ የመንግስት መሪ ሆነ። ለስላሳ ቅደም ተከተል. ኤልዛቤት ተተኪዋን በፍፁም ስለማትጠራት፣ ሲሲል በድብቅ የመቀጠል ግዴታ ነበረባት።[]ስለዚህ ከስኮትላንዳዊው ጄምስ ስድስተኛ ጋር በኮድ ድርድር ውስጥ ገባ፣ እሱም ጠንካራ ነገር ግን እውቅና የሌለው የይገባኛል ጥያቄ ነበረው። ኤልዛቤት እና "የከፍተኛውን ሰው ልብ ጠብቅ፣ ወሲብ እና ጥራት ምንም ነገር ትክክል ያልሆነው እንደ አላስፈላጊ ማብራሪያዎች ወይም በራሷ ድርጊት ብዙ ጉጉ" ነው። ምክሩ ሰራ። የጄምስ ቃና ኤልዛቤትን አስደስቷታል፣ እሷም ምላሽ ሰጥታለች፡- “እንግዲህ እንደማትጠራጠር አምናለሁ፣ ነገር ግን የመጨረሻ ደብዳቤዎችሽ ተቀባይነት ባለው መልኩ ተወስደዋል ምክንያቱም የእኔ ምስጋና የሚጎድላቸው ስላልሆኑ፣ ነገር ግን በአመስጋኝነት መንፈስ አቅርቡልኝ። በታሪክ ምሁር ጄ.ኢ.ኔል እይታ ኤልዛቤት ምኞቷን ለያዕቆብ በግልፅ ተናግራ ላትሆን ትችላለች፣ነገር ግን “የተሸፈኑ ሐረጎች ከሆነ የማይታለሉ” በማለት አሳውቃቸዋለች።በጓደኞቿ መካከል ተከታታይ ሞት እስከ 1602 መኸር ድረስ የንግስት ጤንነት ጤናማ ነበር ። እ.ኤ.አ. በመጋቢት ወር ኤልዛቤት ታመመች እና "በተቀመጠ እና ሊወገድ በማይችል የጭንቀት ስሜት" ውስጥ ቆየች እና ለሰዓታት መጨረሻ ላይ ትራስ ላይ ሳትነቃነቅ ተቀመጠች። ሮበርት ሴሲል መተኛት እንዳለባት ሲነግራት፣ “ትንሽ ሰው ለመኳንንት የምትጠቀምበት ቃል መሆን የለበትም” ብላ ተናገረች። ማርች 24 ቀን 1603 በሪችመንድ ቤተመንግስት ከጠዋቱ ሁለት እና ሶስት መካከል ሞተች። ከጥቂት ሰአታት በኋላ ሴሲል እና ምክር ቤቱ እቅዳቸውን አውጥተው የእንግሊዝ ንጉስ ጀምስ አወጁ። እ.ኤ.አ. በ1750ዎቹ የእንግሊዝ ካላንደር ማሻሻያ ተከትሎ የንግሥቲቱን ሞት በ1603 መመዝገብ የተለመደ ቢሆንም፣ እንግሊዝ መጋቢት 25 ቀን አዲስ ዓመትን ታከብራለች፣ በተለምዶ ሌዲ ቀን በመባል ይታወቃል። ስለዚህም ኤልዛቤት በአሮጌው አቆጣጠር በ1602 የመጨረሻ ቀን ሞተች። ዘመናዊው ኮንቬንሽን አዲሱን ለዓመት ሲጠቀሙ አሮጌውን የቀን መቁጠሪያ ለቀን እና ለወሩ መጠቀም ነው.የኤልዛቤት የሬሳ ሣጥን በምሽት ከወንዙ ወርዶ ወደ ኋይትሃል፣ ችቦ በበራ ጀልባ ላይ ተወሰደ። በኤፕሪል 28 የቀብር ሥነ-ሥርዓቷ ላይ የሬሳ ሳጥኑ በጥቁር ቬልቬት በተሰቀለ በአራት ፈረሶች በተሳለ መኪና ላይ ወደ ዌስትሚኒስተር አቢ ተወሰደ። ታሪክ ጸሐፊው ዮሐንስ ስቶው እንዳሉት፡- ዌስትሚኒስተር በጎዳናዎቻቸው፣በቤታቸው፣በመስኮቶቻቸው፣በመሪዎቻቸው እና በገንዳዎቻቸው ላይ ብዙ አይነት ሰዎች ተጭነው ነበር፣ይህን ለማየት በወጡት፣እናም የእርሷን ምስል በሬሳ ሣጥን ላይ ተዘርግቶ ሲያዩ፣እንዲህ አይነት አጠቃላይ ማልቀስ፣ማቃሰት እና በሰው ትዝታ ውስጥ እንዳልታየ ወይም እንዳልታወቀ ማልቀስ። ኤልሳቤጥ በዌስትሚኒስተር አቢ ውስጥ ታስራለች፣ ከግማሽ እህቷ ሜሪ 1 ጋር በተጋራው መቃብር ውስጥ። በመቃብራቸው ላይ የላቲን ፅሁፍ " ተባባሪዎች & " ወደ "" ተተርጉሟል። መንግሥትና መቃብር፣ እንተኛለን፣ ኤልሳቤጥ እና ማርያም፣ እህቶች፣ በትንሣኤ ተስፋ። ኤልዛቤት በብዙ ተገዢዎቿ አዘነች፣ ሌሎች በመሞቷ ግን እፎይታ አግኝተዋል። የንጉሥ ጄምስ የሚጠበቀው ነገር በጣም ተጀመረ ነገር ግን ውድቅ አደረገ። በ1620ዎቹ የኤልዛቤት አምልኮ ናፍቆት መነቃቃት ነበር። ኤልሳቤጥ የፕሮቴስታንቶች ጀግንነት እና የወርቅ ዘመን ገዥ ተብላ ተወድሳለች። ጄምስ የተበላሸ ፍርድ ቤትን ሲመራ የካቶሊክ ደጋፊ ሆኖ ተሣልፏል። ኤልዛቤት በንግሥና ዘመኗ መጨረሻ ላይ ያዳበረችው የድል አድራጊ ምስል፣ ከቡድንተኝነት እና ከወታደራዊ እና ከኢኮኖሚያዊ ችግሮች ዳራ አንፃር፣ ከጥቅም ውጪ የሆነች እና ስሟ ከፍ ከፍ አለ። የጎልፍሬይ ጉድማን የግሎስተር ኤጲስ ቆጶስ፣ “የስኮትላንድ መንግሥት ልምድ ባገኘን ጊዜ ንግሥቲቱ ሕያው የሆነች ትመስላለች። ከዚያ በኋላ የማስታወስ ችሎታዋ በጣም ከፍ ያለ ነበር።” የኤልዛቤት መንግሥት ዘውድ፣ ቤተ ክርስቲያን እና ፓርላማ በሠሩበት ጊዜ ተስማሚ ሆነ። ሕገ መንግሥታዊ ሚዛን. በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ በፕሮቴስታንት አድናቂዎቿ የተሳለችው የኤልዛቤት ምስል ዘላቂ እና ተደማጭነት ነበረው። የማስታወስ ችሎታዋም በናፖሊዮን ጦርነት ወቅት እንደገና ታደሰ፣ ሀገሪቱ እንደገና በወረራ አፋፍ ላይ ስትገኝ። በቪክቶሪያ ዘመን የኤልዛቤት አፈ ታሪክ በጊዜው ከነበረው የንጉሠ ነገሥታዊ ርዕዮተ ዓለም ጋር ተስተካክሎ ነበር, እና በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ኤልዛቤት ለውጭ ስጋቶች ብሔራዊ ተቃውሞ የፍቅር ምልክት ነበረች. የዚያን ጊዜ ታሪክ ጸሐፊዎች እንደ ጄ.ኢ.ኔል እና ኤ.ኤል. እና ደግሞ በግል ንግሥቲቱን ሃሳባዊ: እሷ ሁልጊዜ ትክክል ሁሉንም ነገር አደረገ; የእሷ ይበልጥ ደስ የማይሉ ባህሪያት ችላ ተብለዋል ወይም እንደ ጭንቀት ምልክቶች ተብራርተዋል. ይሁን እንጂ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ጸሐፊዎች ስለ ኤልዛቤት የበለጠ የተወሳሰበ አመለካከት ወስደዋል. የግዛት ዘመኗ በ1587 እና 1596 በካዲዝ ላይ በተካሄደው ጦርነት በስፓኒሽ ላይ በተሳካ ሁኔታ ወረራ በመፈጸሙ ታዋቂ ነው፣ ነገር ግን አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች በየብስ እና በባህር ላይ ወታደራዊ ውድቀቶችን ያመለክታሉ። በአየርላንድ የኤልዛቤት ጦር በመጨረሻ አሸንፏል። ነገር ግን ስልታቸው መዝገብዋን ያበላሻል። የፕሮቴስታንት ብሔራትን በስፔንና በሐብስበርግ ላይ ደፋር ተሟጋች ከመሆን ይልቅ በውጭ ፖሊሲዎቿ ውስጥ ጠንቃቃ ትሆናለች። ለውጭ ፕሮቴስታንቶች በጣም የተገደበ እርዳታ ሰጥታለች እና አዛዦቿ በውጭ ሀገር ለውጥ ለማምጣት ገንዘብ ሳትሰጥ ቀርታለች። ኤልዛቤት ብሄራዊ ማንነትን ለመቅረፅ የሚረዳ የእንግሊዝ ቤተክርስትያን መስርታ ዛሬም በቦታው ይገኛል። በኋላ የፕሮቴስታንት ጀግና ብለው ያመሰገኗት ሰዎች ሁሉንም የካቶሊክ እምነት ልማዶች ከእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ለማቋረጥ ፈቃደኛ አለመሆኖን ችላ ብለውታል። በእሷ ዘመን ጥብቅ ፕሮቴስታንቶች በ1559 የተካሄደውን የሰፈራ እና የአንድነት ድርጊት እንደ ስምምነት አድርገው ይመለከቱት እንደነበር የታሪክ ተመራማሪዎች አስታውሰዋል። እንዲያውም ኤልዛቤት እምነት የግል እንደሆነ ታምናለች እና ፍራንሲስ ቤከን እንዳሉት “በሰዎች ልብ ውስጥ መስኮቶችን እና ምስጢራዊ ሀሳቦችን መሥራት” አልፈለገችም። ኤልዛቤት በአብዛኛው የመከላከያ የውጭ ፖሊሲን ብትከተልም, የግዛቷ ዘመን የእንግሊዝን የውጭ አገር ደረጃ ከፍ አድርጎታል. ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሲክስተስ አምስተኛ “ሴት ብቻ ነች፣ የግማሽ ደሴት እመቤት ብቻ ነች፣ ሆኖም ግን እራሷን በስፔን፣ በፈረንሳይ፣ በግዛቱ፣ በሁሉም እንድትፈራ ታደርጋለች። በኤልዛቤት ዘመን፣ ሕዝበ ክርስትና እንደተበታተነች ብሔሩ አዲስ በራስ የመተማመን እና የሉዓላዊነት ስሜት አገኘ። ኤልዛቤት አንድ ንጉስ በሕዝብ ፈቃድ እንደሚገዛ የተገነዘበች የመጀመሪያዋ ቱዶር ነበረች። ስለዚህ ሁል ጊዜ ከፓርላማ እና ከአማካሪዎቿ ጋር ትሰራለች እውነቱን ይነግሯታል—የእሷ ስቱዋርት ተተኪዎቿ ሊከተሉት ያልቻሉትን የመንግስት ዘይቤ። አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች እድለኛ ብለው ይጠሩታል; አምላክ እንደሚጠብቃት አምናለች። ኤልዛቤት "ብቻ እንግሊዘኛ" በመሆኗ እራሷን በመታበይ በእግዚአብሔር ታምናለች፣ እውነተኛ ምክር እና የተገዥዎቿ ፍቅር ለአገዛዟ ስኬት። በጸሎቷ እግዚአብሔርን አመሰገነች፡- ጦርነቶች እና ብጥብጦች በአስከፊ ስደት በዙሪያዬ ያሉትን ሁሉንም ነገስታት እና ሀገራት ባናደዱበት ጊዜ፣ የእኔ ንግሥና ሰላማዊ ነበር፣ እና የእኔ ግዛት ለተሰቃየች ቤተክርስቲያንሽ መቀበያ ነው። የሕዝቤ ፍቅር ጸንቶ ታየ የጠላቶቼም አሳብ ከሸፈ።
48823
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%85%E1%88%AD%E1%8C%AB%E1%89%B5%20%E1%8A%B3%E1%88%B5
የቅርጫት ኳስ
የቅርጫት ኳስ ወይም ባስኬትቦል በዓለም ዙሪያ በቡድኖች የሚጫወት የኳስ እስፖርት ነው። ጨወታው በ1885 ዓም በካናዳዊው ዶ/ር ጄምስ ነይስሚስ በአሜሪካ አገር ተፈጠረ። በመላው አለም ተወዳጅነትን ያተረፈ የቡድን ስፖርት አይነት ነው፡፡ ጨዋታው እኤአ በ1891 በካናዳዊው ዶ.ር ጀምስ ኒስሚዝ በአሜሪካ አገር ተፈጠረ፡፡ የቅርጫት ኳስ ወይም ባስኬት ቦል፡፡ ጨዋታው በእጅ የሚከናወን ሲሆን በመሰረታዊነት የ4 መአዘን ሬክታንግል ቅርፅ ያለው መጫወቻ ኮርት 5 ተጫዋቾ ያሉት ሁለት ቡድኖች እና በእጅ የሚወረወረው ድቡልቡል ኳስ ለጨዋታው አስፈላጊ የሆኑ ቁሶች ናቸው፡፡ 5ቱ ተጫዋቾ ሁልጊዜም የተጫዋቾችን ቦታ ይይዛሉ፡፡ ከተጫዋቾቹ በቁመት ረጅም የሆነው ተጫዋች አብዛኛውን ጊዜ የመሀል ቦታ ይይዛል፡፡ እኤአ በ1891 በካናዳዊው የጂም መምህር ጀምስ ኒስሚዝ በስፕንግ ፊልድ ማሳቹስትስ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የተፈጠረው የቅርጫት ኳስ በአሁኑ ሰአት በአለማችን ላይ እጅግ ታዋቂና በመላው አለም በርካታ ተመልካቾች ያሉት የስፖርት አይነት ነው፡፡ የናሽናል ባስኬት ቦል አሶሴሽን ለአለም ፕፌሽናል ባስኬት ቦል በማሳደግና በማስተዋወቅ በክፍያ በተሰጥኦና በውድድር ብቃት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቶለታል፡፡ ከሰሜን አሜሪካ ውጪ ያሉ የብሄራዊ ሊግ መስፈርትን ያሟሉ ታላላቅ ክለቦች ለአህጉራዊ ቻምፒየን ሺፕ እንደ ኢሮሊግ እና አሜሪካ ሊግ የናሽናል ባስኬት ቦል አሶሴሽን አስተዋፅኦ ማሳያ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ የ ባስኬት ቦል ወርልድ ካፕ እና ውድድር ዋና ዋና የአለማቀፍ ዝግጅቶችን እና የብሄራዊ ቡድኑ በርካታ ተጫዋቾችን መሳብ የቻሉ ውድድሮች ናቸው፡፡ የሠውነት ማጎልመሻ ትምህርተ ፕሮፌሽናል በ በአሁኑ መጠሪያው ውስጥ አሰልጣኝ የነበሩት ካናዳዊ ጀምስ ኒስዝ እኤአ ከዲሴምበር 1891 ቀደም ብሎ የጂም ትምህር ቤት ክፍልን በዝናባማ ወቅትም ለማስቀጠል ፈለጉ፡፡ ተማሪዎቹ ክረምቱንም በተሻሎ የሰውነት ጥንካሬ እንዲያሳፉ በሚል በርካታ ሀሳቦች አስበው በኋላም ከበርካታ ሀሳቦች ውስጥ የባስኬት ቦልን በመምረጥ 10 ጫማ ወይም 3 ሜትር ከፍታ ያለው የባስኬት ቦል መረብ መስቀያ አዘጋጁ፡፡ ለባስኬት ቦል መጫወቻ ተብሎ የተዘጋጀው የመጀመሪያ ኳስ ብራውን ወይም ቡናማ ቀለም ሲኖረው እኤአ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ ግን ቶኒ ሂንክል የተባለ ሰው ለተጫዋቾቹ ግልፅ ሆና መታየት አለባት በሚል የኳሷ ቀለም ወደ ብርቱካናማ ቀለም እንዲቀየር አደረገ የተቀየረውም ቀለም እስካሁን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በ1892 ከገና እረፍት መልስ ለመጀመሪያ ጊዜ የባስኬት ቦልን የተጫወተው ፍራንክ ማሀን ሲሆን በወቅቱ ስያሜውን ምን እንደሚሉት ኒስሚዝን ጠየቃቸው እሳቸውም ውድድሩን የማስጀመር ሀሳብ እንጂ ስለስያሜው አላሰብኩበትም ሲሉ መለሱለት፡፡ ፍራንክ ለምን ኒስሚዝ ኳስ አይሉትም ሲል ሀሳብ አቀረበ፡፡ ኒሚዝም ከሳቁ በኋላ እንዲህ አይነት ስያሜዎች ጨዋታውን ይገድሉታል ብለው መለሱለት፡፡ ፍራንክም መልሶ ለምን ባስኬት ቦል አንለውም አለ፡፡ ኒስሚዝም ባስኬት አለን ኳስም አለን ስለዚህ ባስኬት ቦል መባሉ ለኔ ተስማምቶኛል፤ ጥሩ ይመስለኛል ብለው አፀደቁለት፡፡ የመጀመሪያው የባስኬት ቦል ውድድርም ኒዮርክ ውስጥ በሚገኝ ጂምዚየም ውስጥ እኤአ በጃንዋሪ 1892 በ9 ተጫዋቾ ተጀመረ፡፡ በወቅቱ የእግር ኳስ 10 ተጫዋቾ በ1 ቡድን የሚጫወቱበት ወቅት ስለነበር ሀይለኛ የበረዶ ግግር የእግር ኳስ ጨዋታቸውን እንዳያከናውኑ ስላስቸገራቸው ወደቤት ውስጥ ገብተው 10ሩ ተጫዋቾ በሁለት በመከፈል 5 5 ሆነው መጫወት ባስኬት ቦልን ወይም የቅርጫት ኳስን ጀመሩ፡፡ በ1897 -1898 በአንድ ቡድን የተጫዋቾ ብዛት 5 ሆኖ ፀደቀ፡፡ እኤአ በ1980ዎቹ እና በ1990ዎ ውስጥ ፕሮፌሽናል ውድድሮችን በማካሄድ የስፖርቱን ተወዳጅነትና እውቅና ከፍ እንዲል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ እና የምንግዜም ምርጥ የቅርጫት ኳስ ተጫዋቾች የሚባሉት 3 ተጫዋቾ ላሪ በርድ፤ ኢረን ማጂክ ጆንሰን እና ማይክል ጆርዳን ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 17፣1963 በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው ማይክል ጆርዳን በአለማቀፍ ደረጃ ብዙ ሽልማቶችን ተቀዳጅቷል፡፡ ብዙ ሰዎች ከምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሳይሆን መቼም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ተጫዋች ነው በማለት ያሞግሱታል፡፡ ከሴቶች እውቅ የባስኬት ቦል ተጫዋቾች ውስጥ አንዷ የሆነችው የአሜሪካ ፕሮፌሽናል ባስኬት ቦል ተጫዋች ማያ አፕሪል ሞኖር በርካታ የብሄራዊ ቻምፒየን ሺፕን በማሸነፍ የጆን ዎደን አወርድ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ እኤአ በ1932 ስምንት ሀገራት የብሄራዊ ባስኬት ቦል አሶሼሽን አቋቋሙ፡፡ ስምንቱ መስራች ሀገራት አርጀንቲና ፤ ፤ ግሪክ ፤ ጣሊያን ፤ ፤ ፓርቹጋል ሮማንያ እና ሲውዘርላንድ ናቸው፡፡ ሴቶች በባስኬት ቦል ውድድር ላይ መሳተፍ የጀመሩት በ1892 በስሚዝ ኮሌጅ ውስጥ ነበር፡፡ በወቅቱ ሰንዳ በርሶን የተባለች የሰውነት ማጎልመሻ መምህር የኒስሚዝን የባስኬት ቦል ህጎች ለሴቶች እንዲሆኑ አድርጋ አስካከለቻቸው፡፡ በአጭሩ በአዲሱ ስፖርት በመማረኳ ስለውድድሩ ከኒሰሚዝ ብዙ ለመማር ትፈልግ ነበር፡፡ በመጋቢት 21 1893 የመጀመሪያው የሴቶች ባስኬት ውድድርን አዘጋጀች፡፡
51192
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%AE%E1%8A%95%E1%88%B6%20%E1%89%A3%E1%88%85%E1%88%8B%E1%8B%8A%20%E1%8B%A8%E1%8A%A5%E1%88%AD%E1%8A%A8%E1%8A%95%20%E1%88%B5%E1%88%AB
የኮንሶ ባህላዊ የእርከን ስራ
የኮንሶ መልከዓ-ምድር ባህላዊ ዓለም አቀፍ ቅርስ የአስተዳደር ዕቅድ ሰነድ ከለሳ ተካሄደ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን የኮንሶ መልከዓ ምድር ባህላዊ ዓለም አቀፍ ቅርስ የአስተዳደር ዕቅድ ሰነድ አስመልክቶ ለ3 ቀናት በኮንሶ ወረዳ ካራት ከተማ ከሰኔ 25-27 ቀን 2007 ዓ.ም ባዘጋጀው አውደ ጥናት የሰነዱን ክለሳ አደረገ፡፡ አውደ ጥናቱ የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊዎችን ጨምሮ ሳይንቲስቶች ፣የኮንሶ ወረዳ አመራር አካላት ፣የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሙያዎች እና በኮንሶ ወረዳ ከተለያዩ ቀበሌዎች የተዉጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ የኮንሶ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት በአገራችን የኮንሶ ህዝብ የአኗኗር ዘይቤና መገለጫው የሆነው ታታሪነቱን መሰረት በማድረግ በመልከዓ-ምድርና ባህላዊ እሴቶች ጥበቃ በአለም አቀፍ ደረጃ እዉቅና ማግኘቱ የኮንሶ ህዝብ የአገር በቀል ዕውቀት ዉጤት ቢሆንም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ከፍ ያለ የዕውቀት አሻራ ያረፈበት በመሆኑ ለአስተዳደር እቅድ ሰነድ ክለሳው እየተደረገ ላለው ርብርብ አጋዥ ሆናል ብለዋል፡፡ አያይዘውም ሀገራችን ኢትዮጵያ ብዝሃነት ባላቸው ታሪካዊ፣ባህላዊና ተፈጥሮአዊ መስህቦች የተሞላች መሆኗ በአለም አቀፍ ቅርስነት ደረጃ የተመዘገቡ አስር ቅርሶች ፣ የሰው ልጅ መገኛነቷን የሚመሰክሩ በርካታ ቅሬተ አካላት ፣ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች እምቅ የማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶች እና አስደናቂ ባህል፣ቋንቋ እንዲሁም የራስዋ የሆነ የቀን አቆጣጠር ማሳያዎች ናቸው፤ከነዚህም ውስጥ የኮንሶ መልከዓ ምድር ቅርስ ሲሆን ይህ የኮንሶ መልከዓ-ምድር በርካታ ማራኪ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ቅርሶች የያዘ በዋናነትም በውስጡ የተለያዩ ባህላዊ እርከኖች የሚሰሩበት፣በካብ የታጠሩ መንደሮች የተቀለሱበት፣ባህላዊ ጎጆዎን፣ጥብቅ ደኖችን፣ሀውልቶችና ባህላዊ ኩሬዎች የያዘና ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ ከመሆኑ ባለፈ አሁንም ባህላዊ ሂደቱን ጠብቆ እየተጓዘ ያለና የተለያዩ ተመራማሪዎችንና ሳይንቲስቶች ቀልብ የሚስቡ ታሪካዊና ባህላዊ መስህቦቿ የሚደነቁ ሲሆኑ ይህም መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የአገራችን ዘጠነኛ ቅርስ አድረጎ እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ሰኔ 2003 ዓ.ም መመዝገቡ ይታወሳል፤ይሁን እንጂ ቅርሱ ለአለም ህብረተሰብ ከሚሰጠው ፋይዳ አንጻር በአግባቡ ጥበቃና እንክብካቤ በማድረግ እሴቶቹ ሳይቀየሩና ሳይበረዙ ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት ዉስጥ የተጋረጡ የዘመናዊነት አስተሳሰቦች ቅርሱን እንዳይጎዱት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡ በአዉደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ም/ኃካፊ አቶ ለማ መሰለ በበኩላቸዉ የኮንሶ ባህላዊ መልከዓ ምድር በክልሉ መንግስት፣በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ፣በአጋር ድርጅቶች፣በዘርፉ ባለሙያዎች፣በኮንሶ ወረዳ አስተዳደርና የአከባቢው ማህበረሰብ ባደረጉት ከፍተኛ ድጋፍና ጥረት በአለም አቀፍ ቅርሰነት መመዘገብ የኮንሶ ህዝብ ማንነት፣ባህል፣ታሪክ፣የአኗኗር ዘይቤ፣ወዘተ…ከአገራችን አልፎ በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕዉቅና ለማግኘት ያስቻለው ሲሆን የክልሉንና የአገራችን ገጽታ በመለወጥ ረገድም ታላቅ ድርሻ እንዳለው እሙን ነው፤ ይህ ደግሞ በራሱ የዓለም ትኩረትን በመሳብ የኮንሶ ወረዳ ዋና የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን ያደረገ ሲሆን ከጊዜ ወደ ጊዜ አከባቢው ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ምቹ እድል ፈጥሯል፤በተለይም ከቱሪስት ፍሰት መጨመር ጋር ተያይዞ የቱሪስት አገልግሎት መስጫ ተቋማት በአከባቢው እንዲስፋፉ መልካም አጋጣሚም ፈጥሯል፤ይህ ደግሞ የአከባቢው ማህበረሰብ ባህላዊ ዕደ-ጥበብ ምርቶቹን ለገበያ በማቅረብ፣ወደ አከባቢው በሚመጡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በመሳተፍ እና በርካታ ተግባራት ላይ በመሰማራት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን እንዲረጋገጥ አድርጓል፤ ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በቅርሱ ህልዉና ላይ በርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች እየተጋረጡበት ስለሚገኝ ሁሉም ባለድርሻአካላት እነዚህን ቅርሶች ከአደጋ እንዲታደጋቸው ጥሪያቸውን አስተላለፏል፡፡ በዓዉደ ጥናቱም የአለም ዓቀፍ የቅርስ ስምምነት በኮንሶ ዓለም አቀፍ ቅርስ ላይ ያለው ፋይዳ፣ቀደም ሲል የነበረው የአስተዳደር ዕቅድ ሰነድ ዉስጥ የተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች፣የህግ ማዕቀፎች( በደቡብ ብ/ብ/ክ/መ/ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የተዘጋጀ አዋጅ ቁጥር 141/2003 የኮንሶ ባህላዊ መልከዓ-ምድር አለም ዓቀፍ ቅርስ ለመጠበቅ የወጣ አዋጅ)፣በኮንሶ ዓለም አቀፍ ቅርስ የኮንሰርቬሽንና የጥገና ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች፣የኮንሶ ዓለም አቀፍ ቅርስ የቱሪዝም አስተዳደርና የህ/ሰብ ተጠቃሚነት እና የ2003 የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ስምምነትና ለኮንሶ ባህላዊ መልከዓ-ምድር ያለው ፋይዳ በሚሉት ዙሪያዎች ላይ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ወይይት የተደረገባቸው ሲሆን በዋናነትም በአሁኑ ሰዓት የኮንሶ ባህላዊ መልከዓ-ምድር አለም አቀፍ ቅርስ ያለበት ደረጃ ላይ በስፋት ውይይት ተደርጓል፡፡ በዚህም የኮንሶ መልክዓ ምድር በዓለም አቀፍ ቅርስነት ለመመዝገብ ያበቋቸው መስፈርቶች 1ኛ/ ተወዳዳሪ የሌለው ወይም ቢያንስ ለባህላዊ አሰራር ወይም ለአለ ወይም ለጠፋ የሰው ልጆች ስልጣኔ ብቸኛ ማስረጃ በመሆኑ 2ኛ/ ለሰው ልጆች ባህላዊ አሰፋፈር እና የመሬት አጠቃቀም የላቀ ምሳሌ በመሆን የአንድን ህብረተሰብ ባህል የሚወክል የላቀ ምሳሌ በመሆኑ በተለይም ቅርሱ ሊቀለበስ በማይችል ሁኔታ ለጉዳት ለሚያጋልጥ ተጽዕኖ ያልተጋለጠ በመሆኑ እና 3ኛ/ በቀጥታ ወይም በተጨባጭ መንገድ ከሁነቶች ወይም ከህያው ባህል ወይም አስተሳሰብ ወይም እምነት፣ ስነ-ጥበብ ወይም ስነ-ጽሁፍ ጋር በተገናኘ የላቀ ሁለንተናዊ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ማለትም ፡-የቅርሱ የላቀ ሁለንተናዊ እሴት ዓለም-አቀፍ ፋይዳ ስላለው፣ቅርሱ ጥንታዊ ይዘቱን የጠበቀ በመሆኑ ቅርሱ ሙሉዕነቱ በአግባቡ የተጠበቀ ስለሆነ፣ ቅርሱ በቂ ባህላዊ ጥበቃ የሚደረግለት እና የአስተዳደር ሥርዓት የተዘረጋለት መሁኑን ተወስቷል፡፡ከዚሁ ጋር ተያይዞ ቅርሱን ማስመዝገብ በራሱ ውጤት ያለመሆኑ ምክንያቱም የቅርሱን ጥበቃና እንክብካቤ ማረጋገጥ እና ቅርሱን ለዘላቂ ልማት ለማዋል እና ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ቀጣይነት ያላቸውን የአስተዳደር ስራዎችን መስራት አስፈላጊ ይሆናል በማለት ጽሑፍ አቅራቢዎቹ አንስቷል፡፡ በዋናነትም በአሁኑ ወቅት የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ያዘጋጀው የኮንሶ ባህላዊ መልከዓ-ምድር አለም አቀፍ ቅርስ ለመጠበቅ የወጣዉ አዋጅ ቁጥር 141/2003ኝ የሚጻረሩ በርካታ ቅርሱን ሊጎዱ የሚችሉ ድርጊቶች እየተካሄዱ መሆናቸው ለአብነትም፡- መተኪያ የሌላቸዉ የኮንሶ ባህላዊ ጎጆ ቤቶች ፈርሰው በቆርቆሮ መተካታቸው፣ ትክል ድንጋዮችና ዋካዎች እየተነቀሉና እየተሰባበሩ መሆኑ፣ የስልጣን መሸጋገሪያ ምልክትና የቃል ኪዳን መገለጫዎች ልዩ ስያሜ እየተሰጣቸው መምጣት፣ ቅርሶቹ ከኃይማኖት ጋር ማያያዝ፣ በቅርሶቹ ክልል ውስጥ የተለያዩ የልማት ተግባራት ማከናወን፣ ለቅርሶቹ እየተደረገ ያለው ጥበቃና እንክብካቤ አነስተኛ መሆን ፣ መተኪያ የሌላቸው ቅርሶች መሸጥ ወዘተ…ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ ደግሞ በአዋጁ መሰረት የቅርሶቹን ይዘት የሚቀይሩ ማንኛዉንም እንቅስቃሴ መፈጸም ወንጀል ከመሆኑም በተጨማሪ ኮንሶ ከአለም ተምሳሌትነቷ ተሰርዞ የኮንሶ ማህበረሰብ የማንነት ጥያቄዎች፣የቋንቋና የስራ ባህሉና እሴቶች ይጠፋሉ፡፡ ስለሆነም ሁሉም የሚመለከተው አካል ( የኮንሶ ወረዳ የኃይማኖት አባቶች፣ሽማግሌዎች፣ ማህበረሰቡ፣ ተማሪ፣ መምህሩ፣ ሴቶች፣ የፍትህ አካሉ፣ ምክር ቤቶች፣ አስፈጻሚ አካላት ማህበራት ወዘተ …) መክረዉበት፣ሁሉም የራሱ አጀንዳ አድርጎትና የቤት ስራ አድርጎ በመዉሰድ በቀጣይነትም ድጋፍ በሚሹ ጉዳዮች ላይ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት የኮንሶን የተፋጠነ እድገት ለማስቀጠል የድርሻው እንዲወጣ የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች አሳስበዋል፡፡ የማንነታችን መገለጫ የሆኑ ቅርሶቻችን በመጠበቅ አገራችን ኢትዮጵያ የቱሪስት መዳረሻ እናድርጋት!
12795
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%83%E1%8A%95
ብርሃን
ብርሃን ነገሮች በዓይን እንዲታዩ የሚያደርግ የተፈጥሮ ሞገድ ነው። የብርሃን ሞገድ ከኤሌክትሪክ እና ከመግነጢስ የተሰራ ስለሆነ ሞገዱ የ ኤሌክትሮመግነጢስ ጨረራ ይባላል። ይሁንና፣ የኤሌክትሮመግነጢስ ጨረራ ብርሃንን ብቻ ሳይሆን የብርሃንን ታናናሽና ታላላቅ ወንድሞች ሳይቀር ያፈልቃል። ከብርሃን ታናናሽ ወንድሞች፣ ሬዲዮ፣ ራዳር እና ታህታይ ቀይ ይገኙበታል። ታላላቅ ወንድሞቹ ቢባል፣ ላዕላይ ወይን ጠጅ፣ ኤክስ ሬይ፣ ጋማ ጨረር ይገኛሉ። እነዚህ የብርሃን ወንድሞች በተፈጥሯቸው ከብርሃን ጋር አንድ ቢሆኑም ፣ የሰው ዓይን ሊያያቸው ስለማይችል ብርሃን አይባሉም። ሆኖም ግን አንድ አንድ እንስሳት እነዚህን ሞገዶች መመልከት ይችላላሉ። ለምሳሌ ታህታይ ቀይ የሚባለው የብርሃን ታናሽ ወንድም፣ ለሰዎች እንደ ሙቀት ሆኖ ይሰማል። ለምሳሌ የፀሐይ መሞቅ ከምትተፋው የታህታይ ቀይ ጨረራ ይመነጫል። በበረሃ የሚንከላዎሱ እባቦች ይህን ሞገድ በአይናቸው መመልከት ስለሚችሉ፣ ሙቀት ያለውን ማንኛውንም ነገር በጭለማ ሳይቀር ማየት ይችላሉ። ንቦች በተቃራኒ፣ የሰው ልጅ እማያየውን ላዕላይ ወይን ጠጅ ሞገድ በዓይናቸው ማየት ስለሚችሉ፣ አበቦች ለንቦች ከሰው ልጅ የተለየ መልክና መልዕክት ያስተላልፋሉ። ብርሃን ሞገድ ብቻ ሳይሆን፣ እንደሌሎቹ ጨረራዎች የሞገድና እኑስ ሁለትዮሽተፈጥሮን አዋህዶ የያዘ ነው። ስለዚህና ስለመሳሰሉት መሰረታዊ የብርሃን ባህርያት የሚያጠናው የዕውቀት ዘርፍ ሥነ ብርሃን (ኦፕቲክስ) በመባል ይታወቃል። የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት (ፊዚክስ) ምርምር ዋና ክፍል ነው። የብርሃን ጸባዮች፣ ምንጮችና ፋይዳዎች የብርሃን ፍጥነት የብርሃን ፍጥነት ብርሃን በመቅጽበት ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ አይጓዝም። ይልቁኑ ብርሃን የሚጓዘው በከፍተኛ፣ ነገር ግን ውሱን ፍጥነት ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ የብርሃንን ፍጥነት በተሳካ ሁኔታ የለካው ሮመር የተባለ የዴንማርክ ሰው ሲሆን ይህም በ1676 ዓ.ም. ነበር። ከርሱ በኋላ የተነሱ ሳይንቲስቶች፣ በተሻሻለ መንገድ ፍጥነቱን ለክተዋል። በአሁኑ ዘመን የሚሰራበት የብርሃን የኦና ውስጥ ፍጥነት 299,792,458 ሜትር በሰከንድ ነው<>። በሌላ አነጋገር አንድ የብርሃን ጨረር በያንዳንዷ ሰከንድ ወደ ሶስት መቶ ሚሊዮን ሜትር የሚጠጋ ርቀት ይጓዛል። ይህ የጠፈር ውስጥ ፍጥነት በ ምልከት ሲወከል፣ ለተፈጥሮ ህግጋት ጥናት ከፍተኛ ፋይዳ ያለው የተፈጥሮ ቋሚ ቁጥር ነው። ብርሃን፣ ከኦና ወጥቶ በቁስ አካል ውስጥ (ለምሳሌ በአየር ውስጥ) ሲጓዝ ፍጥነቱ ይቀንሳል። የዚህ ቀስተኛ ፍጥነት መጠን በቁሱ ዳይኤሌክትሪክ ባህርይና በብርሃኑ አቅም ይወሰናል። ብርሃን ኦና ውስጥ ያለው ፍጥነት በአንድ ቁስ ውስጥ ላለው ፍጥነቱ ሲካፈል ውጤቱ የዚያ ቁስ የስብራት ውድር ይባላል። በሒሳብ ቋንቋ ሲጻፍ፦ እዚህ ላይ = የቁሱ የስብራት ውድር ሲሆን፣ ደግሞ በቁሱ ውስጥ ያለው የብርሃን ፍጥነት ነው። የብርሃን የጉዞ አቅጣጫ መቀየር ብርሃን በቀጥተኛ መንገድ እንደሚጓዝ ከጥንት ጀምሮ የታዎቀ ሃቅ ነው። ደግሞም የብርሃን ቀጥተኛ ጉዞ አልፎ አልፎ ሊስተጓጎል እንደሚችል ሌላው የሚታዎቅ ሃቅ ነው። ብርሃን የሚጓዝበትን አቅጣጫ በሦስት መንገዶች ይቀይራል፦ እነርሱም በመንጸባረቅ፣ በመሰበር እና በመወላገድ ናቸው። መንጸባረቅ (ሪፍሌክሽን) የብርሃን ነጸብራቅ ብርሃን አንድ ቁስን ሲመታ የቁሱ አተሞች የተወሰነውን ብርሃን ውጠው የተቀረውን መልሰው በተለያየ አቅጣጫ ወደ ውጭ ይረጫሉ። ይህ ጉዳይ የብርሃን መበተን ይሰኛል። ቁስ ነገሮች የመታየታቸው ምስጢር ከዚህ የብርሃናዊ መፍካት አንጻር ነው። ከነዚህ ቁሶች በተለየ መልኩ፣ እንደ መስታውት ያሉ፣ ገጽታቸው ልስልስ የሆኑ አካላት፣ ብርሃን ከገጽታቸው ሲንጸባረቅ በሚነሳው የሞገድ መጠላለፍ ምክንያት አብዛኛው የሚፈካው ጨረራ እርስ በርሱ ይጣፋል። በዚህ መጠፋፋት ወቅት ጸንቶ የሚቀረው፣ ብርሃኑ በአረፈበት ማዕዘን ትክክል ተገልብጦ ያለው የሞገድ ስብስብ ብቻ ነው፣ ይኸውም የብርሃን ነፀብራቅ ይሰኛል። በሌላ አባባል፣ ብርሃን አንድ ገጽታ ላይ ሲያርፍ እና ሲንጸባረቅ በነጸብራቁና በመጤው ጨረር መካከል ያለው ማዕዘን ከሁለት እኩል ቦታ ይከፈላል፣ የሚያካፍላቸውም የገጽታው ቀጤ ነክ ነው። ከዚህ በተጨማሪ በብርሃን ስብረት አማካይነት ብርሃን ሊንጸባረቅ ይችላል። ይህ የሚሆነው አንድ የብርሃን ጨረር ያለበትን አካል ለማምለጥ ያለው ፍጥነት በቂ ሆኖ ሳይገኝ ሲቀር ነው። ጨረሩ የቁሱን ድንበር ከተወሰነ ማዕዘን በላይ በሆነ አቅጣጫ ሲመታ በጣም ከመሰበሩ የተነሳ ተመልሶ ወደ ቁሱ ይንጸባረቃል። ይህም አጠቃላይ ውስጣዊ ነጸብራቅ እሚባለው ነው። የአልማዝ ፈርጦች መጭለቅለቅ ከዚህ የተነሳ ነው። ብርሃን በዘፈቀደ ሲንጸባረቅ ተበተነይባላል። እንደ መስታዎት ነጸብራቅ አቅጣጫን የተከተለ ሳይሆን እንደ ግድግዳ መፍካት ወይንም እንደብርሃን ጸዳል በሚተን ውሃ ውስጥ መፍካት ነው። የሰማይ ሰማያዊ ቀለም የሚመነጨው ብርሃን በከባቢ አየር ስለሚበተን ነው። የደመና እና ወተት ነጭነት እንዲሁ ብርሃን በውሃ እና በካልሲየም ስለተበተነ ነው። ስብረት (ሬፍራክሽን) የብርሃን ስብረት የብርሃን ስብረት እምንለው የብርሃን ጨረር ካንድ ብርሃን አሳላፊ ወደ ሌላ አሳላፊ አካል ሲጓዝ የሚገጥመውን ፈጣን የአቅጣጫ መቀየር ሁኔታ ነው። ይህ የመጉበጥ ሁናቴ በስኔል ህግ እንዲህ ሲባል በሒሳብ ቋንቋ ይገለጻል፦ እዚህ ላይ በብርሃኑ ጨረርና በአንደኛው ብርሃን አስተላላፊ አካል ቀጤ ነክ መካከል ያለውን ማዕዘን ሲዎክል ደግሞ በሁለተኛው አካል ቀጤ ነክና በብርሃኑ ጨረር መካከል ያለውን ማዕዘን ይወክላል። 1 እና 2 የብርሃን አስተላላፊዎቹ የስብራት ውድር ናቸው፣ = 1 ለጠፈር ሲሆን > 1 ደግሞ ለማናቸው ብርሃን አስተላላፊና በከፊል አስተላላፊ ቁስ አካሎች የሚሆን ነው። አንድ ጨረር ከአንድ አካል ወጥቶ ወደሌላ አካል ሲገባ የጨረሩ የሞገድ ርዝመትና ፍጥነት ይቀየራል። ሆኖም ግን ድግግሞሹ ባለበት ይጸናል። ያ ጨረር ለሚገባበት አካል ገላ ቀጤ ነክ ካልሆነ የሞገድ ርዝመቱ ወይም ፍጥነቱ መቀየር ብርሃኑ እንዲጎብጥ ወይም አቅጣጭ እንዲቀይር ያደርገዋል። አንድ መኪና አንድ ጎን ጎማዎቹ ቀጥ ቢሉና ሌሎች ጎን ጎማዎቹ ቢሽከረከሩ ሳይወድ በግድ እንደሚታጠፍ ነው። የብርሃን አቅጣጫ መቀየር የብርሃን ስብረት በመባል ይታወቃል። የተለያዩ የብርሃን ቀለማት እኩል አይሰበሩም። ቀይ ብርሃን ቀስ ብሎ ሲሰበር ወይን ጸጅ ደግሞ በከፍተኛ ሁናቴ ይሰበራል። ስለሆነም ከሁሉም ቀለም የተሰራ ነጭ ብርሃን በብርሃን ሰባሪ አካላት፣ ለምሳሌ ፕሪዝም ወይንም የእስክርፒቶ ቀፎ ውስጥ ሲያልፍ ይበተንና ኅብረ ቀለማትን ይፈጥራል። የቀስተ ደመና መፈጠር ብርሃን በከባቢ አየር ባሉ የውሃ ሞለኪሎች መሰበር ምክንያት ነው። መወላገድ (ዲፍራክሽን) የብርሃን መወላገድ ሞገዶች እንቅፋት ወይም ጠባብ ክፍተት ሲያጋጥማቸው በእንቅፋቱ ዙርያ የመጠምዘም ባህርይ ያሳያሉ። ለምሳሌ ከአንድ ክፍል ሆኖ ከሌላ ክፍል የሚወራን ወሬ ማዳመጥ መቻሉ የድምጽ ሞገድ በግድግዳወችና በሮች ዙሪያ መጠማዘዝ በመቻሉ ነው። ከዚህ በተጻራሪ የዕለት ተለት ተመክሯችን እንደሚያረጋግጥልን ብርሃን በቀጥተኛ መንገድ እንደሚጓዝ ነው፣ ሰሆነም አንድ ክፍል ሆነን ሌላ ክፍል የሚሆነውን ማየት አንችልም። ነገር ግን በጥንቃቄ ስናስተውል ይሄ ሙሉ በሙሉ እውነት ሆኖ አናገኘውም። ለምሳሌ በጣም ስል የሆኑ ጠርዞች የሚያሳርፉትን ጥላ በጥንቃቄ ስንመረምር አንድ ወጥ ከመሆን ይልቅ በፈርጅ በፈርጁ የደመቀና የጨለመ ሆኖ እናገኛለን። ብርሃን በቀጥታ እሚጓዝ ከሆነ ለምን ይሄ ሆነ? አንድ ክፍል ሆነን ሌላ ክፍል የሚሆነውን የማናይበት ምክንያት የብርሃን ሞገድ ርዝመት ከድምጽ ሞገድ ርዝመት በጣም ስለሚያን የድምጽን ያህል መጠማዘዝ ስለማይችል ነው። ብርሃን ሁል ጊዜ በቀጥታ መንገድ አይጓዝም። ይልቁኑ የብርሃን ጨረር እንቅፋት ሲያጋጥመው ወይም ጠባብ ክፍተት ውስጥ ሲገባ ይጎብጣል። ይህ ኩነት የብርሃን መወላገድ ይሰኛል። በጠባብ ቀዳዳዎች አጮልቀን ስንመለከት ነገሮች ተንጋደው የሚታዩት ስለዚህ ምክንያት ነው። ከብርሃን መንጸባረቅና መሰበር ውጭ የብርሃንን አቅጣጫ የሚቀይረው ይሄ መወላገድ ነው። መጠላለፍ (ኢንተርፌረንስ) የብርሃን መጠላለፍ የብርሃን መጠላለፍ እንደማንኛውም ሞገድ መጠላለፍ ነው እንጂ ልዩ አይደለም። ለምሳሌ አንድ የረጋ ውሃ ላይ ሁለት ልጆች የተለያየ ቦታ ላይ ጠጠር ቢጥሉ፣ ከጠጠሮቹ እየከበቡ የሚሰፉት ሞገዶች የሚሰሩት መጠላለፍ አንድ ቦታ በሃይል እንዲጎብጡ፣ ሌላ ቦታ እንዲያንሱ እያደረገ ለአይን የሚስብ የመጠላለፍ ቅርጾች በውሃው ገጽታ ላይ ይሰራሉ። ብርሃንም እንዲህ አይነት የመጠላለፍ ባህርይ ያሳያል። ጉዳዩን በቀላሉ ለማየት የያንግን ሙከራ ማካሄድ ይረዳል። የያንግ ሙከራ ምንድን ነው፣ አንድ አይነት ቀለም ያለው ብርሃን አንድ በቀጭኑ የተሸነተረ ካርድ ላይ ይበራል። ከዚህ ሽንትር ካርድ ብርሃኑ እየተወላገደ ይሄድና ሌላ ሁለት ቦታ ላይ የተሸነተረ ካርድ ላይ እንዲያርፍ ይደረጋል። ከኒህ ሁለት ሽንትሮች ያመለጠው ሁለት ጊዜ የተወላገደ ብርሃን ንጹህ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ ይደረጋል። የብርሃንን መጠላለፍ በደንብ በሚያሳይ መልኩ ይህ የሚያርፈው ብርሃን ብዙ ደማቅና ጨለማ ሸንተረሮች በግድግዳው ላይ ይፈጥራል። ከዚህ በተረፈ የብርሃን መጠላለፍ በተፈጥሮም እንዳለ ለማስተዋል ይቻልል። ለምሳሌ ሥሥ የዘይት ወይም ቤንዚን እድፍ በውሃ ላይ ተንጣሎ ሲገኝ የሚፈጥረው ኅብረ ቀለም ከብርሃን መጠላለፍ የሚመጣ ነው። የሲዲ ገጽታም ኅብረ ቀለም ማሳየቱ ብርሃን መጠላለፍ የሚመነጭ ነው። መዋልት (ፖላራይዜሽን) የብርሃን መዋልት የብርሃን ሞገድ ልከ አንድን ገመደ ወደላይ ወደታች ስናደርግ እንደምናገኘው ሞገድ ነው። ማለት የሞገዱ ጉዞ ወደፊት ሲሆን ሞገዱ የሚርገበገበው ወደ ላይ-ወደ ታች ነው። ሞገዱ የሚርገበገብበት አቅጣጫ የሞገዱ ዋልታ ይሰኛል። የሞገዱ የጉዞ አቅጣጫና የሞገዱ ዋልታ አንድ ወጥ አይደሉም። ይልቁኑ ሞገዱ በአንድ አቅጣጫ እየተጓዘ እያለ የሞገዱ ዋልታ ሊቀየር ይችላል። ለምሳሌ የአንድ ሞገድ ዋልታ ወደ ላይ ወደታች ከሆነ፣ ይህን ቀይሮ ወ ጎንና ወደ ጎን ሊርገበገብ ይችላል። ይህ የብርሃን ባህርይ መዋልት ይባላል። ጉዳዩን በገሃዱ አለም ማየት ይቻላል። ብዙ የጸሐይ መነጽሮች የሚሰሩት ብርሃንን ዋልታ ከሚለዩ ንጥር ነገሮች ነው። ስለሆነም የመነጽሮቹ መስታወቶች የሚያሳልፉት ከነርሱ ዋልታ ጋር የሚስማማውን ክፍል ብቻ ነው። ስለዚህ ሁለት የጸሓይ መነጽሮችን በተለያየ ማዕዘን በማስቀመጥ ከአንዱ ያለፈውን የዋለታ ብርሃን በሌላው መነጽር እንደገና በማጥራት የተለያየ የብርሃን መጠን እንዲያልፍ ማድረግ ይቻላል። በርግጥ ሁለቱ መነጽሮች ደርቦ በማስቀመጥና አንዱን ከሌላው አንጻር በማዞር ከከፍተኛ ብርሃን እስከ ሙሉ በሙሉ ጨለማ እንዲያስተላልፉ ማድረግ ይቻላል። የብርሃን ግፊት ብርሃን በተጨባጭ ግፊት ማድረግ ይችላል። ይህን የሚያደርገው ፎቶኖች የተሰኙት የብርሃን እኑሶች የቁስን ገጽታ በመደብደብ ግፊታቸውን በማሳረፍ ነው። የብርሃን ግፊት እሚለካው የአንድን ብርሃን ጨረር ሃይል ለብርሃን ፍጥነት በማካፈል ነው። የብርሃን ፍጥነት እጅግ ግዙፍ ስለሆነ ክብርሃን የሚገኘው ግፊት በጣም አንስተኛ ነው። ስለዚህ አንዲት ሳንቲም በብርሃን ለማንሳት 30 ቢሊዮን የ1 ዋት ሌዘር ፖይነተሮች በአንድ ላይ መሳተፍ አለባቸው፡፡ የሆኖ ሆኖ የብርሃን ግፊት በናኖ ሜትር ደረጃ ባለው አንስተኛው አለም ውስጥ የማይናቅ ሚና ይቻወታል። ስለሆነም ጥቃቅን የናኖ ሜትር ማብሪያ ማጥፊያወችን በብርሃን ግፊት ለመቆጣጠር ጥናት ይካሄዳል። ብርሃንና የኬሚካል ፋይዳው አንድ አንድ ቅመሞች (ኬሚካልስ) ብርሃን ሲያርፍባቸው ጠባያቸው ይቀየራል። ግማሾቹ የብርሃኑን አቅም ገንዘብ በማድረግ ከፍተኛ አቅም ገዝተው ከሌላ ቁስ ጋር የኬሚካል ግንኙነት ያደርጋሉ፣ ገሚሶቹ ያላቸውን ግንኙነት አቋርጠው ለብቻቸው ይሆናሉ። የተክሎች ምግብ ዝግጅት (ፎቶ ሲንቴሲስ) ከዚህ ወገን ነው። እፅዋት የተለያዩ የስኳር አይነቶች የሚሰሩት ከውሃ፣ የተቃጠለ አየርና ከብርሃን ነው። የሰው ልጅ ቆዳ እንዲሁ ቫይታሚን ዲ የሚፈጥረው የብርሃንን አቅም በመጠቀም ነው። ዓይንም ብርሃንን የሚመለከተው ከአይን ውስጥ ያሉ ኬሚካሎችን በብርሃን የመቀየር ጠባይ በመጠቀም ነው። የፎቶ ፊልም እንዲሁ ከብርና-ናይትሮጅን ኬሚካል የተሰራ ሲሆን ብርሃን ሲያርፍበት ጠባዩን ስለሚቀያይር ፎቶ ለማንሳት ያስችላል። የብርሃን ምንጮች ብዙ የብርሃን ምንጮች በአለም ላይ ይገኛሉ። ብዙ ጊዜ የብርሃን ምንጮች በመጋል የፋሙ ነገሮች ናቸው። ማናቸውም ሙቀት ያላቸው ነገሮች የጥቁር አካል ጨረራ ያመነጫል። ለምሳሌ የፀሐይ አካል ገጽታ ሙቀት መጠን 6,000 ኬልቪን ሲደሰርስ በዚህ ምክንያት ከገጽታው የሚመነጨው የፀሐይ ጨረራ ለአይን የሚታይ ብርሃንንም ይጨምራል። ብስሌት እንደተደረሰበት ከፀሐይ ጨራራ ወደ 40% ይሚጠጋው በአይን የሚታይ ብርሃን ነው። በዚህ ትይዩ የቤት አምፑል ከሚወስደው የኤሌክትሪክ አቅም በብርሃን መልኩ የሚረጨው 10% ብቻ ነው፣ የተቀረውን ወደ ግለት ቀይሮ በታህታይ ቀይ ጨረራ ይረጫል። የሚግም የፋመ ብረትም ብርሃን ክሚያመነጩ ወገን ነው። መለስተኛ ሙቀት ያላቸው ነገሮች፣ ለምሳሌ የሰው ልጅ፣ ለአይን የማይታይ የጥቁር አካል ጨረራ በአካባቢው ይረጫል፣ ሆኖም ይሄ በታህታይ ቀይ ደረጃ ስለሆነ ለአይን አይታይም። ሙቀቱ እየጨመረ ሲሄድ ከታህታይ ቀይ የሞገድ ርዘመቱ ቀንሶ ወደ ቀይ ቀለም እያደላ ይሄዳል። የጋመው ቀይ የበለጠ ሲግል ወደ ነጭ ቀለም ይቀየርና ሙቀቱ እየባሰ ሲሄድ ወደ በጣም አጭር የሞገድ እርዝመተ እያደላ ይሄዳል፣ ይሄውም ወደ ሰማያዊ ቀለም መሆኑ ነው። ከዚህ ይብስ ከጋለ አንድኛውን ላይን ይሰወርና የላዕላይ ወይነ ጸጅ ጨረር ባህሪን ይይዛል። እኒህን ቀለማት በሚንቀለቀል እሳት ውስጥ የሚፍሙ ብረታ ብርቶችም ሊስተዋሉ ይችላሉ። አተሞች ብርሃንን አመንጭተው መርጨት ወይም ውጠው ማስቀረት ይችላሉ። ይህን እሚያረጉት እንዲሁ በደፈናው ሳይሆን ለጠባያቸው በሚስማማ አቅም ውስጥ ያለን ብርሃን ነው። ይህ ሲሆን አተሞቹ የመርጨት መስመር በአተሞቹ ብትን ላይ እንዲፈጥር ያደርጋል። ሁለት አይነት የኤሌክትሮማግኔቲክ ምርጨት አለ። ፩ኛው ድንገተኛ መርጨት ሲባል ይህ አይነት ብርሃን በብርሃን ረጪ ዳዮድ፣ ጋዝ ርጭት፣ ኒዖን አምፑል፣ ሜርኩሪ አምፑልና በ እሳትነበልባል ለሚመነጨው ብርሃን ተጠያቂ ነው። ፪ኛው የተነሳሳ መርጨት ሲባል በሌዘር እና ሜዘር ለሚመነጨው ብርሃን ተጠያቂ ነው። የኤሌክትሪክ ቻርጅ ተሸካሚ አካላት (ለምሳሌ ኤሌክትሮን )፣ የሚጓዙበት ፍጥነት ሲቀንስ ጨረራ ይረጫሉ፣ በዚህ አኳኋን የምታይ ብርሃን ሊፈጥሩ ይችላሉ፡ ሳይክሎትሮን ጨራራ፣ ሲንክሮትሮን ጨራራ እና ብሬምስትራንግ ጨራራ የዚህ ምሳሌወች ናቸው። አንድ አንድ እኑሶች (ፓርቲክልስ) በቁስ አካል ውስጥ ከብርሃን ፍጥነት በላይ ከተጓዙ ቼርንኮቭ ጨረራ የተሰኘን በአይን ሊታይ የሚጭል ጨረር ይፈጥራሉ። አንድ አንድ ቅመሞች (ኬሚካሎች) ብርሃን የመፍጠር ችሎታ አላቸው። ህይወት ባላቸው ነገሮች፣ በተለይ በአንድ አንድ ትንኞች፣ ዘንድ ብልጭ-ድርግም የሚል ብርሃን እንዲያመነጩ የሚያግዛቸው ይሄው ነው። አንድ አንድ ቁስ አካላት ከፍተኛ አቅም ባለው ጨረራ ሲደበደቡ የመጋምና የመፍካት ሁኔታ ያሳያሉ። ይህ ጉዳይ ፍሎሮሰንስ ይሰኛል፣ የሸምበቆ መብራት የዚህ አይነት ነው። ሌሎች ደግሞ ቶሎ ከመፍካት ይልቅ ቀስ ብለው ብርሃን መርጨት ያደርጋሉ፣ እኒህ ፎስፎረሰንስ ይሰኛል። ፎስፎረሰንስ ቁሶች በጥቃቅን የአተም ንዑስ አካላት ሲደበደብ እንዲሁ ብርሃን ይሰጣል። በዚህ መንገድ ብርሃን ከሚሰጡት ውገን ፣ የቴሌቪዥን፣ ኮምፒውተር እና ካቶድ ጨረር ቱቦ ይገኙበታል። ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች የብርሃን ማመንጫ መንገዶች አሉ ግን ከላይ የተጠቀሱት ዋና ዋናወቹ ናቸው። ለመሆኑ ብርሃን ምንድን ነው?? ስለብርሃን የተሰነዘሩ ኅልዮቶች በየዘመኑ ጥንታዊት ሕንድ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ6-5ኛ ክፍለ ዝመን የነበሩ ህንዶች ስለብርሃን ብዙ ተፈላስፈዋል። አንድ አንዶቹ ብርሃን ያልተቆራረጠ ነገር ነው ሲሉ ሌሎች ደግሞ የተቆራረጠ እኑስ ነገር ሲሆን ከከፍተኛ ፍጥነት ካላቸው የእሳት እኑሶች የሚፈጠር ነው ብለው አስፍረዋል። ሌሎች በተራቸው ብርሃን የአቅም አይነት ነው ሲሉ የአሁኑን አይነት የፎቶን ግንዛቤ አስፍረዋል። ጥንታዊት ግሪክ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ5ኛው ክፍለ ዝመን ይኖር የነበር ኢምፐዶክልስ እንዳስተማረ የሰው ልጅ አይን ከአራቱ ንጥረ ነገሮች (እሳት፣ አየር፣ መሬትና ውሃ) የተሰራ ሲሆን ጣዖቷ አፍሮዳይት የሰውን ልጅ እሳት በአይኑ ውስጥ እንዳቀጣጠለች፣ ስለዚህም የሰው ልጅ አይን የብርሃን ምንጭ እንደንበር አስተምሯል። ሆኖም የሰው ልጅ ማታ ላይ ስለማያይ ይህ አስተሳሰቡ እንደማያዋጣው በመገንዘብ በርግጥም የሰው ልጅ እሚያየው ከራሱ በሚያመነጨው ብርሃንና ከጸሃይ በሚያገኘው ጨረር ግንኙነት ነው ለማለት ችሏል። ዩክሊድ በበኩሉ የኢምፐዶክልስን ኅልዮት ጥያቄ ውስጥ በመጣል ብርሃን ከአይን ይመነጫል የሚለውን ሃሳብ አልተቀበለም። በተጨማሪ ብርሃን በቀጥተኛ መስመር እንደሚጓዝና ከገጽታ ላይ ሲንጸባረቅ የሚከተለውን የጂዎሜትሪ ህግ አስቀምጧል። ሉክሪተስ በበኩሉ ብርሃን የእኑስ አካላት ውጤት ነው የሚለውን ሃሳብ አስተጋብቷል። ቶሎሚ ደግሞ ስለ ብርሃን መሳበር ጽፏል። አካላዊ ኅልዮት (ዘመናዊ) ከጥንቶቹ በኋላ የአረቡ አል ሃዘን፣ ፈረንሳዩ ደካርት እንዲሁም እንግሊዙ ቤከን እርስ በርሳቸው በሂደት እየተተራረሙ የብርሃንን ምንነት ለማወቅ ሞክረዋል። ሆኖም ደካርት የብርሃንን ጸባይ በአካላዊ መንገድ (ያለ መንፈሳዊ መንገድ) ለመግልጽ ስለቻለ የዘመናዊ የብርሃን ትምህርት አባት በመባል ይታወቃል። የዘመናዊው የብርሃን ኅልዮት ከሁለት የብርሃን ተፈጥሮ ደጋፊወች ቅራኔ ያደገ ነው። አንደኛው ወገን ብርሃን እኑስ (ጠጣር፣ ደቂቅ፣ ፓርቲክል) ነው ሲል፣ ሌላኛው ደግሞ ብርሃን ሞገድ (ዌቭ፣ ፈሳሽ ዓይነት፣ የማይቆራረጥ) ነው የሚል ነበር። እኑስ ኅልዮት እኑስ ስንል እዚህ ላይ ደቂቅ ጠጣር አንስተኛ ነገር እንደማለት ነው። ከነደካርት ቀጥሎ ከፍተኛውን እርምጃ ወደፊት የወሰደው ፒር ጋሲንዲ ብርሃን በጣም ጥቃቅን እኑሶች ክምችት ነው በማለት አስረዳ። ኢሳቅ ኒውተን ገና በወጣትነቱ የጋሲንዲን ጥናት በማንበቡ እርሱም የብራሃንን እኑስነት መሰረት በማድረግ ጥናት አቅርቧል። ለዚህ ምክንያቱን ሲያቀርብ ሞገዶች፣ ለምሳሌ የድምጽ ሞገድ በቀጥታ ከመሄድ ይልቅ በእንቅፋት ዙሪያ መጓዝ ይችላሉ። ነገር ግን ብርሃን በቀጥታ እንጂ እንቅፋትን የመዞር ችሎታ የለውም። ኒውተን የብርሃን ነጸብራቅንና ጥላን በዚሁ ኅልዮቱ ለመግለጽ ችሏል። የብርሃን ስብረትንም በተሳሳተ መልኩ በዚሁ ኅልዮቱ ገልጿል። ኢሳቅ ኒውተን በነበረው የገነነ ክብር ምክንያት 18ኛው ክፍለ ዘመን የርሱን የብርሃን እኑስ ኅልዮት በመከተል ተጠናቀቀ። ይሁንና በ19ኛው ክፍለ ዘመን ይህን አስተሳሰብ የሚቃወሙና የብርሃንን ሞገደኝነት የሚያስተምሩ ጥናቶች መታየት ጀመሩ። ሞገዳዊ ኅልዮት በኒውተን ዘመን የተነሱት ሮበርት ሁክ እና ክርስቲያን ሁይገንስ የብርሃንን ሞገዳዊነት የሚያስረግጡ ጥናቶችን አሳተመው ነበር። ነገር ግን ኒውተን ከነበረው ክብር አኳያ ብዙወች ችላ ብለዋቸው ነበር። የብርሃን ሞገዳዊ ኅልዮት ብርሃን ልክ እንደ ድምፅ እንደሚጠላለፍ የተነበየ ነበር። በ19ኛው ክፍለ ዘመን የተነሳው ቶማስ ያንግ ይህን ጉዳይ በሙከራ ለማሳየት ቻለ። በተረፈ እንደማንኛውም ተራማጅ ሞገድ እንደሚዋልት በዚህ ወቅት በሙከራ ተረጋገጠ። ያንግ በዚህ ሳይወሰን ብርሃን እንደሚወላገድ በሁለትዮሽ ሽንትር ካርድ ሙከራ ለማሳየት ቻለ። የተለያዩ ቀለማት መፈጠር ምክንያቱ በተለያዩት የብርሃን ሞገዶች ውስጥ ባለ የሞገድ ርዝመት ምክንያት እንደሆነ በጥናቱ አቀረበ። ይህ ሁሉ የብርሃንን ሞገዳዊነት ያጠናከረ ጥናትና የብርሃንን እኑስ አለመሆን ለጊዜው ሳይንቲስቶች ያሳመነ ነበር። ላዮናርድ ኦይለር፣ ኦግስቲን ፍሬስነል፣ ሲሞን ፖይሰን የብርሃንን ሞገድ የሂሳብ ቀመሮች ሊጠረጠር በማይችል ሁኔታ መሰረት ሰጡት። ፍሬስነል በ1821 የብርሃን ዋልታዊነት በሞገድ ኅልዮት ብቻና ብቻ የሚገለጽ እና እንዲሁም ብርሃን ተራማጅ ሞገድ እንጂ ፊት-ኋላ የሚል ሞገድ ቅንብር እንዳልሆነ በሂሳብ ቀመሩ ለማስረገጥ ቻለ። ይህ እንግዲህ የኒውተንን የእኑስ ኅልዮት ጥያቄ ውስጥ የጣለ ሂደት ነበር። እንደ ኒውተን ኅልዮት፣ የብርሃን ጨረር ከቀላል ነገር ወደ ጭፍግ (ዴንስ) ያለ ነገር ሲሻገር በግስበት ምክንያት ፍጥነቱ ይጨምራል። ሆኖም ግን ላዮን ፎካልት በ1850 ባደረገው ጥንቃቄ የተመላበት የፍጥነት ልኬት፣ ብርሃን እንዲያውም ጭፍግ ያለ አካል ውስጥ ሲጓዝ ቀስ እንደሚል አረጋገጠ ። ይህ እንግዲህ የኒውተን እኑስ ኅልዮት ሙሉ በሙሎ እንዲጣልና የሞገድ ኅልዮቱ ተቀባይነት እንዲያገኝ ያደረገ ሁናቴ ነበር። የሞገድ ኅልዮት በራሱ ድክመት ነበረው። ድምጽ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ለመጓዝ በመሃከሉ ሞግዱን ተሸካሚ አካል ያስፈልገዋል። ለምሳሌ አንድ ሰው በጠፈር ውስጥ ቢናገር በሌሎች አይሰማም ምክንያቱም የድምጹን ሞገድ የሚያስተላልፍ አየር የለምና። ልክ እንዲሁ ብርሃንን አስተላላፊ አካል ያስፈልጋል። ነገር ግን ብርሃን በባዶ ጠፈር ውስጥ ከፀሐይ መንጭቶ መሬት ይደርሳል። ስለሆነም የጥንቶቹ ሳይንቲስቶች ጠፈር ውስጥ የሚኖር ኤተር የተባለ በአይን የማይታይ ነገር ሞገዱን እንደሚያስተላልፍ መላ ምት አደርጉ። ኮረንቲና መግነጢስ (ኤሌክትሮማግኔቲክ) ኅልዮት ሚካኤል ፋራዳይ በ1845 ዓ.ም. የብርሃንን ዋልታ በመግነጢስ መቀየር እንደሚቻል አስተዋለ። ። ይህ እንግዲህ ብርሃን ከኮረንቲና መግነጢስ ጋር ግንኙነት እንዳለው ያሳየ የመጀመሪያው መረጃ ነበር። ይሄው ፋራዳይ ከ2 አመት በኋላ ብርሃን በጣም ከፍተኛ ድግግሞሽ ያለው ኤሌክትሮመግነጢሳዊ ረብሻ እንደሆነ ጻፈ። በፋራዳይ ስራ ተመስጦ ቀጣዩን ጥናት ያካሄደው ጄምስ ክላርክ ማክስዌውል በ1862 ዓ.ም. ባወጣው ጥናቱ፣ የኤሌክትሮማግኔቲክ ሞገዶች (ማዕበሎች) አንዴ ከተፈጠሩ በኋላ ያለምንም እርዳታ በኅዋ ውስጥ በቋሚ ፍጥነት መጓዝ እንዲችሉ አሳየ። በሂሳብ ቀመሩ እንዳሰላ ይህ የኤሌክትሮመግነጢሳዊ ሞገድ ፍጥነት ሌሎች ሳይንቲስቶች በሙከራ ካገኙት የብርሃን ፍጥነት ጋር አንድ ሆነ። ከዚህ ተነስቶ፣ ማክስዌል፣ ብርሃን የኤሌክትሮማግኔቲክ ሞገድ እንደሆነ አስረዳ። በ1873ዓ.ም. ማክስዌል የብርሃንና የኤሌክትሮማግኔትን ባህርይ እንዲሁም የመግነጢስ መስክንና የኤሌክትሪክ መስክን ጠባይ በሂሳብ ቀመር ግልጽ አድርጎ አስቀመጠ። ሄኔሪክ ኸርዝ በበኩሎ የማክስዌልን ሂሳብ በመጠቀም የራዲዮ ሞገድን ላብሯረተሩ ውስጥ በመፍጠርና በመጥለፍ እንዲሁም ልክ እንደ ብርሃን ሞገዶቹ የመንጸባረቅ፣ መሳበር፣ መወላገድና መጠላለፍ ባህርያትን እንደሚያሳዩ በተጨባጭ በማረጋገጥ የብርሃንን ኤሌክትሮመግነጢሳዊ ሞገድነት ሙሉ በሙሉ አሳማኝ በሆነ መልኩ አረጋገጠ። በአውሁኑ ወቅት እንደሚታወቀው የኤሌክትሮመግነጢሳዊ ማዕበል ከኤሌክትሪክና መግነጢስመስኮች የተሰራ ሲሆን እኒህ መስኮች እርስ በርሳቸው ቀጤ ነክ ናቸው። የማክስዌል ኅልዮትና የኸርዝ ሙከራወች ራዲዮ፣ ራዳር፣ ቴሌቪዥን፣ ገመድ አልባ ግንኙነት እንዲፈጠሩ አደርጉ። ልዩ አንጻርዊ ኅልዮት ልዩ አንጻርዊ ኅልዮት የሞገድ ኅልዮቱ በጣም የተሳካ ከመሆኑ የተነሳ አብዛኛውን የብርሃን እይታዊና ኤሌክትሮመግነጢሳዊ ባህርይ ለመተንተን ያስቻለ ነበር። ይህም የ19ኛው ክፍለ ዘመን ፊዚክስ ታላቁ ድል ተደርጎ ይቆጠራል። ነገር ግን በክፍለ ዘመኑ መዝጊያ ወራት ልዩ ልዩ፣ በሙከራ የተጋለጡ ተቃርኖወችና በኅልዮቱ አጥጋቢ ሁናቴ ሊተነተኑ የማይችሉ የብርሃን ክስተቶች ብቅ ማለት ጀመሩ። አንደኛውና ዋና እራስ ምታት የነበረው የብርሃን ፍጥነት ነበር። የጥንቱ ሳይንቲስት ጋሊልዮ ጋሊሊ እንዳስረዳ ማናቸውም ፍጥነት አንጻራዊ ነው። ስለሆነም አንድ ሰው የሚንቀሳቀስ መኪና ላይ ቢረማመድ ፍጥነቱ የርሱ የመራመድ ፍጥነት ሲደመር የመኪናው ፍጥነት ነው። ነገር ግን የማክስዌል ቀመር ያስረዳ እንደነበር የብርሃን ፍጥነት ምንጊዜም ቋሚና አንድ ነው። ለምሳሌ በሚነዳ መኪና ፊት ያሉ መብራቶች የሚያመነጩት ብርሃን ፍጥነት ከቆመ መኪና ብርሃን ጋር እኩል ነው። ይህ እንግዳ ውጤት በሚኬልሰን ሞርሌ ሙከራ የተረጋገጠ የውኑ አለም ባህርይ ነበር። በ1905 አልበርት አይንስታይን ይህን እንቆቅልሽ እስከፈታ ድረስ እንቆቅልሽ ሆኖ ቆይቶ ነብር። አይንስታይን እንዳስረዳ፣ ኅዋና ጊዜ ቋሚ ነገር ሳይሆኑ የሚለጠጡና የሚኮማተሩ ነገሮች ናቸው። ስለዚህ የብርሃን ፍጥነት (በጠፈር) ምንጊዜም ቋሚ የመሆኑ ምስጢር የኅዋና ጊዜ መኮማተር እንደሆነ አስረዳ። በዚያውም አይንስትያን ከዚይ በፊት የማይታወቀውን የግዝፈት እና የአቅምን ተመጣጣኘት በሚከተለው ቀመሩ አስረገጠ ፡ ማለቱ አቅም ሲሆን፣ የዕረፍት ግዝፈት እና ደግሞ የብርሃን ፍጥነት በጠፈር ውስጥ ናቸው። የእኑስ ኅልዮት እንደገና ማንሰራራት በሙከራ ከተደረሰበት ሌላ እንግዳ ጠባይ በአሁኑ ዘመን የፎቶኤሌክትሪክ ተጽዕኖ የሚባለው የብርሃን ፀባይ ነበር። ብርሃን ከብረታ ብረቶች ገጽታ ጋር ሲገናኝ የገጽታውን ኤሌክትሮኖች ከአተሞቻቸው በማፈናጠር የኤሌክትሪክ ጅረት(ከረንት) እንዲፈጠር ያደርጋል። በጥንቃቄ በተደረጉ ሙከራወች መሰረት የተፈናጣሪወቹ ኤሌክትሮኖች አቅም በሚያርፍባቸው የብርሃን ድምቀት (ኢንተንስቲ) ሳይሆን የሚወሰነው በብርሃኑ ድግግሞሽ መጠን ነበር። እያንዳንዱ አይነት ብረታብረት ከተወሰነ የድግግሞሽ መጠን በታች ያለ ብርሃን ካረፈበት ከነጭርሱኑ ኤሌክትሮኖቹ አይንቀሳቀሱም (የፈለገ ብርሃኑ የደመቀ ቢሆንም)። እኒህ ተስተውሎወች (የሙከራ ውጤቶች) የብርሃንን የሞገድነት ተፈጥሮ የሚቃረኑ ነበሩ። ለብዙ አመታት ሳይንቲስቶች እኒህን ተቃርኖወች ከሞገድ ኅልዮት ጋር ለማስታረቅ ሞክረዋል፣ ነገር ግን አልተሳካላቸውም። አልበርት አይንስታይን በ1905 ዓ.ም. ለችግሩ መፍትሔ አቀረበ። ይህን ያደረገው የብርሃንን እኑስ ኅልዮት እንደገና እንዲንሰራራ በማድረግ ነበር። ሆኖም ግን ለሞገድ ኅልዮት እጅግ ብዙ መረጃ ስለነበር በመጀመሪያ የአይንስታይን መፍትሔ በዘመኑ በነበሩ ሳይንቲስቶች ዘንድ ተቀባይነት አልነበረውም። ነገር ግን የ የፎቶኤሌክትሪክ ተጽዕኖን የአይንስታን ትንታኔ በበቂ ሁኔታ ስለገለጸ ቀስ በቀስ ተቀባይነትን አገኘ፣ ስለሆነም አይንትስታን ለዚህ ስራው የኖቤል ሽልማትን አገኘ። ይህ የአንስታይን የፎቶኤሌክትሪክ ኅልዮት ለቀጣዩ የኳንተም ኅልዮት መሰረትና አሁን ተቀባይነት ላለው የብርሃን ሁለት ጸባይነት መሰረት የጣለ ነበር። ኳንተም ኅልዮት ኳንተም ኅልዮት በ19ኛው ክፍለ ዘመን ከተደረጉ ሙከራወች የተነሳ ሌላ ቀውስ ተፈጠረ፣ ይኸውም የኤሌክትሮማግኔቲክ ኅልዮት በሚለውና በተጨባጭ ሙከራወች ውጤት መካከል የነበር ልዩነት ነው። ማናቸውም ሙቀት ያላቸው ቁሶች የሙቀት ጨረራ ይረጫሉ፣ ነገር ግን ጨረራቸው ያልተቆራረጠ አልነበርም። በ1900፣ ማክስ ፕላንክ የተሰኘው ጀርመናዊ ተማሪ የዚህን ጉዳይ ስረ መሰረት ለማወቅ ባደረገው ጥናት ማናቸውም ነገሮች (ጥቁር አካላት) ኤሌክትሮማግኔት ጨረራ የሚረጩት በጠጣር በጠጣር ቁርጥራጭ እንጂ በተቀጣጣይ እንደፈሳሽ አለነበረም። እኒህ ጠጣር የኤሌክትሮማግኔት ጨረራ ቁራጭ መሰረቶች ፎቶን ተባሉ። የሚይዙት ጠጣር ቁራጭ አቅም ኳንታ እንዲባል አንስታይን አሳወቀ። ፎቶን መባሉ በዚሁ ዘመን ኤሌክትሮኖች እና ፕሮቶኖች የታወቁበት ዘመን ስለነበር ለመለየት ነበር። ፎቶን አቅም ሲኖረው, መጠኑም ከአለው ድግግሞሽ, ,ጋር ቀጥተኛ ውድር አለው። በሒሳብ ሲቀመጥ ማለቱ፦ የ ፕላንክ ቋሚ ቁጥር, የሞገድ ርዝመት፣ እና ደግሞ የብርሃን ፍጥነት ናቸው። ልክ እንዲሁ፣ የፎቶን እንድርድሪት (ሞመንተም) '' ከሞገዱ ድግግሞሽና ጋር ቀጥተኛ ውድር ሲኖረው ከየሞገዱ ርዝመት ጋር ግን ተገልባጭ ውድር አለው። ወደሒሳብ ቋንቋ ሲተረጎም፦ ይሁንና ይህ የፕላንክ ጥናት የፎቶንን ጠጣር የሚመስል ባህርይ በአጥጋቢ ሁኔታ የገለጸ አልነበረም። የእኑስ ሞገድ ሁለትዮሽ የብርሃንን ተፈጥሮ የሚገልጸው የአሁኑ ዘመናዊ ኅልዮት በአልበርት አይንስታይን የፎቶኤሌክትሪክ ተጽዕኖ ኅልዮትና በማክስ ፕላንክ የፎቶን ጥናት ላይ የተመሰረት ነው። የአይንስታን ትንታኔ በእኑስነት ላይ ያተኮረ ሲሆን የፕላንክ ደግሞ በሞገድነት ላይ ያተኮረ ነበር። የዘመናዊው ኅልዮት እሚለው ብርሃን የሞገድ-እኑስ ሁለትዮሽ ተፈጥሮ አለው ይላል። ማለቱ ብርሃን፣ ሞገድም፣ እኑስም ነው። አይንስታይን እንዳስተማረ፡ የፎቶን አቅም ከፎቶኑ ድግግሞሽ ጋር ቀጥተኛ ውድር አለው ( ማለት ድግግሞሹ ሲበዛ፣ አቅሙም ይበዛል፣ ሲያንስ ያንሳል)። ይህ ሃልዮት ሲሰፋ ማናቸውም የአለም አካላት እኑስም ሞገድም ናቸው ብሎ ያስቀምጣል። ብርሃን ብቻ ሳይሆን፣ ማንኛውም ነገር የእኑስነቱን ወይም ደግሞ የሞገድነቱን ባህርይ ለይቶ ሊያወጣ የሚችል ሙከራ ሊካሄድበት ይችላል። አንድ ነገር ግዝፈቱ ትልቅ ከሆነ የእኑስነቱ ባህርይ ገኖ ይወጣል። ስለሆነም የአለምን ሞገዳዊነት በዘልማድ ለማወቅ አስቸጋሪ ነው። ሉዊ ደ ብሮይ በ1924 አፍረጥርጦ የኤሌክትሮንን የእኑስና ሞገድ ሁለትዮሽ ፀባይን እስከተነተነ የሁለቱ ጸባይን የያዘ ብርሃን ብቻ ነው ብሎ ሳይንቲስቶች ያስቡ ነበር። የኤሌክትሮን ሞገዳዊ ባህርይ በ1927 ዓ.ም. በዳቪሰንና ገርመር በተጨባጭ ተመክሮ ተረጋገጠ። ኳንተም ሥነ ኤሌክትሮ-እንቅስቃሴ (ኤሌክትሮዳይናሚክስ) የኳንተም መካኒካል ኅልዮት በብርሃንና ኤሌክትሮማግኔቲካዊ ጨረራ ያለው አስተሳሰብ ቀስ በቀስ እየተቀየረ 1920ወቹ አልቀው 1930ዎቹ ተደግሙ። በ1940ወቹ ይህ ኅልዮት አብቦ አሁን የሚታወቀውን የኳንተም ኤለክትሮዳይናሚክስ () ወይንም በሌላ ስሙ የኳንተም መስክ ኅልዮት ወለደ። ይህ አዲሱ ኅልዮት በብዙ ሙከራወች የተፈተነና ጸንቶ የቆመ ሲሆን በሌላ ጎን ስፋት ያላቸውን የተፈጥሮ ክስተቶች በአጥጋቢ ሁኔታ መተንተን የሚያስች ሆኖ እስካሁን ጸንቶ ይገኛል። ኳንተም ኤሌክትሮዲናሚክስን ያቋቋሙት ሳይንቲስቶች ሪቻርድ ፌይማን፣ ፍሪማን ዴይሰን፣ ጁሊያን ሽዊንገር፣ እና ሽን-ኢችሮ ቶሞናጋ ናቸው። ፌይማን፣ ሽዊንገር እና ቶሞናጋ የ1965 ኖቤል ሽልማት ስለዚህ ስራቸው አሸንፈዋል።