query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
2
300
passage
stringlengths
78
8.98k
category
stringclasses
7 values
link
stringlengths
28
740
⌀
negative_passages
listlengths
5
5
d766d08de2964491ac978054749e6b64
1dee20ef7f798a5f4f9393c780beb163
አትሌቶች ፈታኙን ጊዜ እንዴትይወጡታል?
በአትሌቲክስ ስፖርት ዝና እና ክብሯን የገነባችው ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችንም አግኝታበታለች። ስፖርቱ አንድ የስራ ዘርፍ በመሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣት አትሌቶችን ያቅፋል። አትሌቶችም በዓለም አቀፍ ውድድሮች ሲሳተፉ ከውጤት ባሻገር የውጭ ምንዛሪን በማስገኘት የሀገሪቷን ኢኮኖሚ ያግዛሉ። በሚያፈሱት መዋዕለ ነዋይም ለበርካቶች የስራ እድል ፈጥረዋል። እንደሚታወቀው በዚህ ወቅት ይህ ዘርፍ እንደሌሎች ስፖርቶች ሁሉ ለውድድር ዝግ ሆኗል። ማልዶ ለልምምድ ይወጣ የነበረውና በዓመት ውስጥ ተደጋጋሚ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ የነበረው እረፍት የለሽ አትሌትም ከተላላፊው ቫይረስ ጋር ተያይዞ ከቤት ውሏል። በብሄራዊ ቡድን የተያዙ፣ በተለያዩ ክለቦች የተካተቱ እንዲሁም የአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ተቋማት ሰልጣኝ የሆኑ አትሌቶችም እንዲበተኑ ተደርጓል። በግላቸው የሚሰለጥኑትም ቢሆን እንደ ቀድሞው ከመኖሪያቸው ርቀው የማይጓዙበት ሁኔታ ተጋርጦባቸዋል። ለአንድ ዓመት የተራዘመውን ኦሊምፒክ ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ ቻምፒዮናዎች ላይ ተሳታፊ ለመሆን በብሄራዊ ቡድን የተካተቱ አትሌቶች ደግሞ ከሌሎች በተለየ ሁለት አማራጮችን ያስተናግዳሉ። የመጀመሪያው ለተላላፊው የኮሮና ቫይረስ ተጋላጭ ላለመሆን በሚደረገው የቤት ውስጥ ቆይታ ከልምምድ በመራቃቸው የአቋም መውረድን ማስተናገድ ነው። ሌላኛው ደግሞ የውድድሮችን መራዘም እንደ መልካም እድል በመጠቀም በተደጋጋሚ ውድድር ላይ ያሳለፉ አትሌቶች እንደ ማገገሚያ ጊዜ በመመልከት በተሻለ ብቃት ለመመለስ የራሳቸውን ጥረት ማድረግ ነው። በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ስፖርተኞች ከስፖርቱ ላለመራቅ ምን ማድረግ አለባቸው፣ ፌዴሬሽኑስ ሚናውን በምን መልኩ እየተወጣ ነው ለሚለው በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የአትሌቲክስ ህክምና ከፍተኛ ባለሙያና እና የጸረ አበረታች ቅመሞች ተጠሪዋ ቅድስት ታደሰ ከአዲስ ዘመን ጋር ቆይታ አድርገዋል። የመጀመሪያው ነገር ስነ-ልቦና መሆኑን ባለሙያዋ ይገልጻሉ።በዓለምና በሃገር በመጣው በዚህ ቫይረስ ምክንያት በቤታቸው እስኪቆዩ ድረስ ኦሊምፒክን ጨምሮ ለዚህ የውድድር ወቅት በዝግጅት ላይ የነበሩ አትሌቶች በጥሩ አቋም ላይ ነበሩ። በዚህም ምክንያት አቋማቸው እንዳይወርድና ጂምናዚየሞችም በመዘጋታቸው በቤት ውስጥ የተለያዩ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ ይገደዳሉ። ከትንፋሽ ጋር በተያያዘ ያለውን ደግሞ የሰዎች ንክኪ በሌለበት በግላቸው ጫካ አካባቢ መስራት ይችላሉ። ይህም ወቅታዊ ብቃታቸው እንዳይወርድ እንጂ ለውድድር በሚደረግ ልክ አይሆንም። ይህ እንዲሆን ደግሞ አስቀድሞ እንደተገለጸው ዋናው ነገር በመልካም ስነ-ልቦና ላይ መገኘት መሆኑን ይጠቁማሉ። በማብራሪያቸውም ‹‹የሰው ልጅ በተፈጥሮው በጭንቀት ወቅት ሰውነቱ በሚሰጠው ግብረመልስ የተለያዩ ቅመሞችን ስለሚያመነጭ ለውጥረትና ለመደበት ስሜት ይጋለጣል። አትሌትሌቲክስ የሙሉ ጊዜ ስራው የሆነው አትሌትም ውድድሮች ከሌሉ በእንዲህ ዓይነቱ ሁኔታ ውስጥ ሊገባ ይችላል። ይህ እንዳይከሰትም አትሌቶች ራሳቸውን በስነ-ልቦና ማዘጋጀት ይገባቸዋል›› ሲሉ ያስረዳሉ ባለሙያዋ። ሁኔታዎችን አእምሮ ሲቀበል ሌሎች አካላትን ማዘዝ ስለሚቻል ስነ-ልቦና የመጀመሪያውና ዋነኛው ጉዳይ ነው። ከዚህ ባሻገር በአትሌቲክስ ስፖርት የሚፈራው ነገር ክብደት መጨመር ነው። በክብደት ተወስነው እንደሚካሄዱት የቦክስና የማርሻል አርት ስፖርቶች ሁሉ የረጅም ርቀት በአትሌቲክስም ክብደት መጨመር የራሱ አደጋ ይኖረዋል። በመሆኑም የቡድን እና ጫና ያላቸውን ልምምዶችን በማስቀረት ሰውነትን ባለበት እንዲቆይና የብቃት መዋዠቅ እንዳይከተል የሚያደርግ መሆን እንዳለበት ባለሙያዋ ያስገነዝባሉ። አመጋገብ ላይም አትሌቶች የራሳቸውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባቸዋል፤ አመጋገብ ከሚወጣው ኃይል ጋር ተመጣጣኝ መሆን ይኖርበታል። በዚህ ወቅት ቀለል ያሉ ልምምዶችን እየሰሩ እንደ ወትሯቸው የሚመገቡ ከሆነ ግን ሰውነት ያንን ለማስተናገድ ስለሚከብደው የክብደት መጨመር ይከሰታል። በመሆኑም ይህንን መከታተልና ከቻሉ በየዕለቱ ያሉበትን ሁኔታ በመመዝገብ ማስታወሻ እንዲይዙ ይመከራል። የዓለም አትሌቲክስም በየወቅቱ የሚያወጣውን መረጃ መከታተልም አስፈላጊ ነው። በዚህ ሂደት ሊዘነጋ የማይገባው ዋናው ነገር በቤት ውስጥ የሚሰሩ ማሳሳቢያዎችና ሌሎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች ንጹህ አየር ባለበት ስፍራ መሆኑን ማረጋገጥ ነው። ሰው የማይበዛበትና ነፋሻማ አየር ባለበት ስፍራ ቢንቀሳቀሱ ደግሞ የተሻለ ይሆናል። እንደ ዓለም አትሌቲክስ መረጃ ከሆነ አትሌቶች በተለይም የረጅም ርቀት ሯጮች ትንፋሻቸው የዳበረ በመሆኑ ከሌላው በተለየ ተጋላጭነታቸው የሰፋ ይሆናል። በመሆኑም ራሳቸውን ለየት ባለመልኩ መጠበቅ ይኖርባቸዋል። ፈሳሽ በብዛት መውሰድና በሽታን ሊቋቋሙ የሚችሉ ምግቦችንም ከዚህ ቀደሙ በተሻለ ሁኔታ ማዘውተርና በዓለም የጤና ድርጅት እንዲሁም ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርን ከመሳሰሉ ተቋማት የሚወጡ መረጃዎችን መከታተል ለአትሌቱ ጠቃሚም ነው። ምክንያቱም አብዛኛው የማህበራዊ ትስስር ገጾችን የሚጠቀም እንደመሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙበት መንገድ በራሱ ጎጂ ሊሆን ይችላል። ይህንንና መሰል ግንዛቤዎችን ከማስጨበጥ አንጻር ባለሙያዎች አትሌቱን በአካል ለማግኘት አዳጋች በመሆኑ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተለያዩ ስራዎችን እንደጀመረም ባለሙያዋ ይጠቁማሉ። የፌዴሬሽኑ አመራሮች ባደረጉት ውይይት አትሌቱ ከአዲስ አበባ ውጪ ባሉ ክልሎችም የሚገኝ እንደመሆኑ ሁሉንም ተደራሽ ለማድረግ በቴሌቪዥንና በሬዲዮኖች መልዕክቶችን ማስተላለፍ የተሻለ አማራጭ ሆኖ አግኝቶታል። በመሆኑም ሰፊ ሽፋን ካላቸውና ከክልል የመገናኛ ብዙሃን ጋር በመተባበር፤ አትሌቱ ልምምዱን እንዴትና በምን ሁኔታ መስራት እንዳለበት በባለሙያዎች ግንዛቤ የሚሰጥ ይሆናል። ከዚህ ባሻገር ከወቅታዊው ሁኔታና ከቫይረሱ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን፣ ስነ- ምግብ፣ ስፖርታዊ ስነ-ልቦና፣ የስፖርት ህክምና፣ የመረጃ ክትትል ምን መምሰል አለበት የሚሉና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ነባራዊ ሁኔታውን ባገናዘበ መልኩ ለአትሌቱ እንዲደርስ ይደረጋል። በዚህ ሁሉ ሁኔታ ውስጥ ግን መዘንጋት የሌለበት ዋነኛ ጉዳይ አበረታች ቅመም መሆኑን ያሳስባሉ። ይህንን ግንዛቤ የሚሰጡትም በስፖርቱ ላይ ለረጅም ጊዜ ያሳለፉ ባለሙያዎች እና ኦሊምፒክን ጨምሮ በተለያዩ መድረኮች ላይ ስኬታማ የሆኑ አንጋፋና ተምሳሌት አትሌቶች ሲሆኑ፤ መልእክቶችን፣ ምክሮችንና በተግባር የታገዙ እንቅስቃሴዎችንም ለአትሌቶች የሚያስተላልፉ ይሆናል። ከፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት እንዲሁም ከስልጠና ጥናትና ምርምር ክፍል ጋር በመሆንም በተለያዩ የማህበራዊ ገጾች መልእክቶችን ለማስተላለፍም በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኙ ባለሙያዋ ጨምረው ገልጸዋል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 5/ 2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=30273
[ { "passage": "የመጨረሻ ክፍልባለፈው ሳምንት የስፖርት ማህደር አምዳችን በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ትልቅ ስፍራ የሚሰጣቸውን የ1960 እና 1964 የሮምና ቶኪዮ ኦሎምፒኮችን በተመለከተ ከአበበ ቢቂላ ታሪካዊ የማራቶን ተከታታይ ድሎች ባሻገር ያልተሰሙና ያልተነገሩ ወጎችን ማንሳታችን ይታወሳል። በተለይም ከሮም ኦሎምፒክ የአበበ ቢቂላ የባዶ እግር ገድል ባሻገር የኦሎምፒክ ቡድኑ ገና ከስፍራው ከማቅናቱ አንስቶ በድል እስኪመለስ ድረስ ከመድረክ ጀርባ የነበሩትን ወጎችና ቡድኑ የገጠመውን አጠቃላይ ፈተና በስፋት ዳሰናል። ቀጣዩን የቶኪዮ 1964 ኦሊምፒክን የተመለከቱ ወጎችን ለማቅረብም ለዛሬ ቀጠሮ በያዝነው መሰረትም እንደሚከተለው ለንባብ አሰናድተናል። ቶኪዮ ኦሎምፒክ 1964 ወደ 1964 የቶኪዮ\nኦሎምፒክ የሚጓዘው ቡድን\nበቢሾፍቱ ከተማ አየር\nሃይል በትብብር በሰጠው\nካፕ በተለየ መልኩ\nሲዘጋጅ ቢቆይም ወደዚህ\nኦሎምፒክ ለመጓዝ ምክኒያት\nየሆነው የሮም ኦሎምፒክ\nባለድሉ አበበ ቢቂላን\nችግሮች ይፈታተኑት ነበር።\nበዚሁ ዝግጅት ወቅት\nአበበ ወድቆ በእጁ\nላይ ጉዳት ደርሶ\nነበር። ይህን ዜና\nየሰሙ የውጪ አገር\nመገናኛ ብዙሃንም ወሬውን\nተቀባበሉት። አበበ ቢቂላ\nበቶኪዮ ኦሎምፒክ እንደማይወዳደርም\nፃፉ። ይሁን እንጂ\nአበበ ቀላል ጉዳት\nእንደደረሰበት ፊት ለፊት\nወጥቶ አስተባበለ። የኦሎምፒክ\nጉዞው መዳረሻ ላይ\nግን ሌላ ከባድ\nችግር ገጠመው። አሰልጣኙ\nኦኔ ኔስካነን በአበበ\nላይ የተለየ ነገር\nማስተዋል ከጀመሩ ሰነባብተዋል።\nአበበ ልምምድ ጀምሮ\nያቋርጣል፣ ሲቀመጥና ሲነሳ\nወንበር ይደገፍም ነበር፣\nከመኝታውም እንደ ቀድሞው\nቀልጠፍ ብሎ መነሳት\nአልሆነለትም፣ ይባስ ብሎም\nውድድር እያቋረጠ እስከ\nመውጣት ደረሰ። ይህንን\nያስተዋሉት ቡድን መሪው\nይድነቃቸው ተሰማና ስዊድናዊው\nአሰልጣኝ ኦኔ ኔስካነን\nአበበ ቢቂላ ሕክምና\nመሄድ እንዳለበት ተስማምተው\nወደ ምኒልክ ሆስፒታል\nወሰዱት። የጤና ምርመራው\nውጤት ግን ብዙዎችን\nያስደነገጠ ሆነ። አበበ\nትርፍ አንጀት እንዳለበትና\nበአስቸኳይ የቀዶ ጥገና\nካላደረገ ሕይወቱ አደጋ\nላይ እንደሚወድቅ መነገሩ\nስጋት ፈጠረ። ይህ\nጉዳይ በሚስጥር ቢያዝም\nእያደር ገሃድ መውጣት\nጀመረ። ይድነቃቸውና ኔስካነን\nበጉዳዩ ላይ መከሩ።\nአበበም ቀዶ ጥገናውን\nለማድረግ ተስማማ። የሕክምና ክፍሉና ሌሎች ወገኖች ግን ሦስት ሳምንት ለቀረው ውድድር አበበ ቀዶ ጥገና ማድረግ እንደሌለበት አቋም ያዙ። ይድነቃቸውና ኔስካነን ግን በራሳቸው ሃላፊነት ወስደው ቀዶ ጥገናው እንዲደረግ ወሰኑ። በሁለቱ ሰዎች ላይ ‹‹ኢትዮጵያ በቶኪዮ ኦሎምፒክ የምታገኘውን ወርቅ አስነጠቁ›› በሚል ክስና ወቀሳ ተሰነዘረባቸው። አበበ በሆስፒታል ተኝቶ የሚያሳይ ፎቶ ግራፍ በመውጣቱም የዓለም መገናኛ ብዙሃን አበበ በውድድሩ እንደማይሳተፍ መዘገብ ጀመሩ። በአዲስ አበባ የነበሩ የዜና ወኪሎች አበበ ከቡድኑ ጋር በዝግጅት ላይ ስለሌለ በውድድሩ እንደማይሳተፍ ማረጋገጫ አገኙ። በጉዞው መጨረሻ አበበ ከቡድኑ ጋር ቢጓዝም ህመም ላይ ስለነበረ ጋቢ ለብሶ የተሻለ ህክምና ለማድረግ እንጂ በውድድሩ ላይ ይሳተፋል የሚል እምነት አልነበረም። በቶኪዮ ኦሎምፒክ የተጓዘው 16 ሰው ሲሆን ለዝግጅት የወጣው 80ሺ ብር ብቻ ነው። ማራቶን የሚካሄደው በውድድሩ መዝጊያ ዕለት በመሆኑ አበበ ከህመሙ ለማገገም በቂ ጊዜ አገኘ። አበበ በውድድሩ መሳተፉ እንደታወቀ ብዙዎችን አስገረመ። ቀዶ ጥገና አድርጎ ቁስሉ ሳይጠግ መወዳደሩ ማሸነፍ ከመቻሉ ሌላ በጤናው ላይ ትልቅ ጉዳት እንደሚያመጣ ተዘገበ። የጤና ባለሙያዎች የኢትዮጵያን ልዑካን ቡድን አበበን ለውድድር ማቅረባቸው በሕይወቱ ላይ እንደፈረዱ ሆኖ ተነገረ። በዚህ መሃል ደግሞ አንድ ሰው ብቅ አለ። ሰውየው አሴክ የተባለ የስፖርት ጫማ አምራች ድርጅት ባለቤት ናቸው። ድርጅቱ ግን የሚታወቅ አልነበረም። ይህ ድርጅት ለአበበ ጫማ ሰርቶ እንደሚያቀርብ ነገራቸው። የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ግን ለጫማ መግዣ የሚሆን ገንዘብ እንደሌላቸው ገለፁ። ባለቤቱ ግን በነፃ መሮጫ ጫማውን እንደሚያቀርብ ተናገረ። ነፃ መሆኑን የሰሙት የኛ ሰዎች ‹‹እንደዚያማ ከሆነ ልኩን ውሰድና ሰርተህ ስጠን›› አሉት። ብዙ መላምት ሲሰጥበት የነበረውና ከሕመሙ በቅጡ ያላገገመው አበበ ውድድሩን ማሸነፉ ተዓምር ሆነ። በሽተኛው ሰው ጤነኞቹን ማሸነፉ ብቻ ሳይሆን የዓለም ክብረወሰን ማሻሻሉ ‹‹ ይሄ ሌላ ፍጡር እንጂ ሰው አይደለም›› እስኪባል ተደነቀ። የጤና ባለሙያዎቹም ያዩትን ነገር ማመን ከብዳቸው መጀመሪያም ቢሆን አልታመም ወደሚል ድምዳሜ ደርሰው ቀዶ ጥገና ማድረጉን እስከመጠራጠር ደረሱ። የቶኪዮውን ኦሎምፒክ ለየት\nየሚያደርገው አፍሪካውያን የነፃነት\nአየር መተንፈስ በጀመሩበት ወቅት ላይ መደረጉ ነው። ብዙ የአፍሪካ አገራት ከቅኝ ግዛት ወጥተው በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት፣ ለመወዳደር ብቻ ሳይሆን ወደ ነፃነት ሜዳ የመጡበትም መድረክና ዓለምን የተቀላቀሉበት ስፍራ ነበር። በኦሎምፒክ መድረክ የመጀመሪያቸው በመሆኑ የጥቁር ኩራትና ተምሳሌት በሚሉት አበበ ቢቂላ የይቻላል መንፈስ ተቀርፀው ነበር። ብዙዎቹ የአፍሪካ አገራት የመጀመሪያቸው ኦሎምፒክ በመሆኑ በማራቶን ውድድር እንደ አበበ ቢቂላ በባዶ እግር የሮጡበት አጋጣሚም በታሪክ ይታወሳል። በቶኪዮ ኦሎምፒክ ከአበበ ቢቂላ ሌላ ማሞ ወልዴ በአስር ሺ ሜትር ወርቅ ማምጣት የሚችልበት እድል በቀላ የቴክኒክ ስህተት ሳይሳካ ነገር ግን ትልቅ ትምህርት የተገኘበት ነበር። በፍፃሜው ውድድር የተጠበቁት የአሜሪካና የአውስትራሊያ አትሌቶች ነበሩ። ማሞ ስለተፈጠረው ነገር ሲናገር‹‹ እንደማሸንፋቸው እርግጠኛ ነበርኩ፣ እስከ መጨረሻ ዙር አብረን ነበርን፣ ሁለቱ ከእኔ ፊት ነበሩ፣ የቱኒዚያው ጋሙዲ ከእኔ ቀጥሎ ነው፣ ከእኔ ፊት የነበሩት ሁለቱም ትንፋሽ ጨርሰዋል፣ የመጨረሻ መቶ ሜትር ላይ ደርሰን አምልጬ ለመሄድ ተዘጋጀሁ፣ አሜሪካዊው አትሌት የመጨረሻው መቶ ሜትር መታጠፊያ ላይ እየተጠመዘዝኩ አውስትራሊያዊው አትሌት በክርኑ ደቆስ አድርጎ ወደ ኋላ እንድቀር በማድረግ አምልጦ ለመውጣት ነበር የተዘጋጀው፣ እኔ ደግሞ በሁለቱ መሃል በተፈጠረው ክፍተት አምልጬ ለመሄድ ስል ለእነሱ የተሰነዘረው ክርን እኔን መቶኝ ተደናቅፌ ወደኩኝ፣ ያን ጊዜ ሁሉንም አጣሁ፣ ከኋላ የነበረው ቱኒዚያዊ አትሌት የነሐስ ሜዳሊያውን ወሰደ፣ ከውድድሩ በኋላ ከአበበ ጋር ስነጋገር ስህተት መስራቴን አወኩኝ፣ እኔ መሄድ የነበረብኝ በሦስተኛው መስመር ነበር። ›› ይላል። በአስር ሺ ሜትር የማሞ ስህተት ለኢትዮጵያውያን ማስተማሪያ የሆነው የቶኪዮው ኦሎምፒክ ሆኖ ከዚያ በኋላ በርቀቱ ቅርፅ ማስያዝ የተቻለበት አጋጣሚ ተፈጥሯል። የቶኪዮ ኦሎምፒክ ከተጠናቀቀ\nበኋላ ቡድኑ ወደ\nአዲስ አበባ ከመመለሱ\nበፊት ጃፓኖች ማወቅ\nየፈለጉት የአበበን የአሸናፊነት\nሚስጥር ነበር። በሽተኛ\nሆኖ አርባ ሁለት\nኪሎ ሜትር የሮጠበት\nሚስጥር። በዚህ የተነሳ\nበጃፓን ስርዓተ ትምህርት\nበሞራል ትምህርት ውስጥ\nአበበ ቢቂላን የሚመለከት\nምዕራፍ እንዲካተት አደረጉ።\nይህም ማኛውንም ነገር\nከግብ ለማድረስ ፅናት\nማስፈለጉን ለዚህም አበበን\nምሳሌ ማድረጋቸው ነው።\nበሮም ኦሎምፒክ በባዶ\nእግሩ ማሸነፉ፣ በቶኪዮ ከሕመሙ ሳያገግም ጤነኞቹን ማሸነፉ ተምሳሌት መሆኑን ‹ፅናት› ካለ ሁሉንም ነገር ማድረግ እንደሚቻል ጃፓኖች ያስተምሩበታል። ከውድድሩ በኋላ አበበን የሚመለከቱ ሁለት ነገሮች ተከስተዋል። አበበ ህመምተኛ በመሆኑ ጋቢ ለብሶ ነበር ወደ ጃፓን የተጋዘው። በወቅቱ በአገራችን አንድ ሰው ከታመመ ጋቢ መልበሱ የተለመደ ነው። ጃፓናውያንም ከውድድሩ በኋላ ለማስታወሻነት ጋቢውን አስቀርተውታል። ለዚህም ምክኒያት ነበራቸው፣ እነሱ ቱሪዝምን በአግባቡ ስለሚጠቀሙበትና አበበም በውድድሩ መነጋገሪያ ስለነበረ ቱሪስቶች ጋቢውን ለብሰው ፎቶ ግራፍ እንዲነሱ ያደርጉበታል። ሌላው አስገራሚ ነገር አበበ የጣት ቀለበቱ ባረፈበት ሆቴል መጥፋቱ ነበር። ቀለበቱ ከሮም ድል በኋላ ከቀዳማዊ ሀይለስላሴ የተበረከተለት ነበር። የቀለበቱ መጥፋት በመገናኛ ብዙሃን ጭምር ተነገረ። በቀለበቱ ላይ የተፃፈው ‹‹ሮም 1960›› የሚልና የንጉሱ ፊርማ ያረፈበት መሆኑ በመገለፁ ለፈላጊዎቹ ብዙም አላስቸገረም። አበበ የወቅቱ ዝነኛና የእነሱም እንግዳ በመሆኑ ጃፓናውያን ወርቁን አፈላልገው መገኘቱን አበሰሩት። የቶኪዮ ልዑካን ቡድን ወደ አገሩ ሲመለስ በአበበ ቢቂላ ድል አዲስ አበባ በአቀባበሉ ደምቃ ነበር። የክቡር ዘበኛ ኦኬስትራ (የአበበ ክፍል) ዝነኛ ሙዚቀኞች ጥላሁን ገሰሰና እሳቱ ተሰማ ‹‹በጣም ደስብሎናል ምኞታችን ሞላ፣ አሸንፎ መጣ አበበ ቢቂላ›› በሚል ያዜሙት ለአቀባበሉ ትልቅ ድምቀት ነበር። የቶኪዮ ኦሊምፒክ ማራቶን የተካሄደው ጥቅምት 11 ቀን 1957 ነበር። ሕዝቡ ድሉን በሬዲዮ ዜና ሰማ እንጂ ምንም ያየው ነገር አልነበረም። ነገር ግን ሚያዝያ 23 1957 የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስርጭት የጀመረበት ጊዜ በመሆኑ በጃፓን ኤምባሲ ትብብር አበበ ሲሮጥና ሲያሸንፍ የታየበት አጋጣሚ ተፈጥሯል። ቶኪዮ አበበን ምን ጊዜም አትረሳውም። ዘንድሮ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት በኮሮና ቫይረስ ስጋት የተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ የአዘጋጅነት እድሉን ለማግኘት ጃፓን አበበ ቢቂላን ‹ዳግም አበበን ለማግኘት› በሚል ለቅስቀሳ ተጠቅማበታለች። የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ በትምህርት ቤት ሩጫ ተሳታፊ በነበሩበት ወቅት የአበበ አድናቂና በአበበ ቅፅል ስም የሚጠሩ እንደነበሩም ከራሳቸው አንደበት ተሰምቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአራትና አምስት ዓመታት በፊት አዲስ አበባ በመጡበት ጊዜም የአበበን ቤተሰቦች ጎብኝተዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 12/2012", "passage_id": "5147af55bab3a9bb76e821f976a100e1" }, { "passage": " ኦ ሊምፒክ ከጤና ስጋት ጋር የተያያዘ ባይሆንም በተለያዩ ጊዜዎች የመሰረዝና የቦታ ለውጥ ሲደረግበት ታይቷል፡፡ እኤአ የ1916 የበጋ ኦሊምፒክ በጀርመን በርሊን ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት በአንደኛ የዓለም ጦርነት ሳቢያ ተሰርዟል:: በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅትም የ1940 የክረምት ኦሊምፒክና የ1944 የበጋ ኦሊምፒክ ውድድሮች የመሰረዝ እድል ገጥሟቸዋል:: እኤአ የ1976 የክረምት ኦሊምፒክም በዴንቨር ኮሎራዶ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የኮሎራዶ ግዛት ሕዝብ ለውድድሩ የሚወጣውን ወጪ በመቃወሙ ውድድሩ የቦታ ለውጥ ተደርጎበት በአውስትራሊያ ኢንስብረክ ለመካሄድ ተገዷል፡፡ ዩ ኤስ ኤ ቱዴይ በወቅቱ እንደዘገበው የኮሎራዶው ኦሊምፒክ የቦታ ለውጥ እንዲደረግበት ውሳኔ ላይ የተደረሰው ውድድሩ ከመካሄዱ ከሦስት ዓመታት አስቀድሞ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ኦሊምፒክ በታሪክ ተራዝሞ የሚያውቅበት አጋጣሚ አልነበረም:: ዓለም በአሁኑ ወቅት እየተሸበረችበት በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ግን የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለአሥራ ስድስት ወራት ሲራዘም በታሪከ የመጀመሪያው ለመሆን በቅቷል፡፡ ይህም ለዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴና ለውድድሩ አዘጋጆች አዲስ ተሞክሮ ብቻ ሳይሆን አዲስ ፈተና ይዞ መምጣቱ አልቀረም፡፡ ይህን አዲስ ፈተናም ለመጋፈጥና ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ከወዲሁ ለማስተካከል ዓለም አቀፍ ኮሚቴውና አዘጋጆቹ ከወዲሁ ሌት ከቀን እየሰሩ እንደሚገኙ ሰሞኑን ገልፀዋል፡፡ የኦሊምፒክ ስፖርቶች ዳይሬክተሩ ክሪስቶፍ ዱቢ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ‹‹ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ውስብስብ ብቻ ሳይሆን አዲስ ፈተና ገጥሞናል›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከጃፓን መንግሥት ጋር በመሆን ይህን ፈተና ለመወጣትና አሁን ዝግጁ የሆኑ ነገሮችን ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ተግባራዊ እንዲሆኑ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ ይህም ማለት ኦሊምፒኩ ከመራዘሙ አስቀድሞ በተያዘለት ጊዜ እንዲካሄድ ዝግጁ የነበሩ የኦሊምፒክ መንደሮችን፣አርባ አንድ ዋነኛየውድድር ቦታዎች፣ ከአርባ ሺ በላይ የሆቴል ክፍሎች፣ከሁለት ሺ በላይ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶችን እንዲሁም አገልግሎትና በሺዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ ቁሶችን ለማቅረብ የተደረጉ ውሎችን መልክ ማስያዝና ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ተግባራዊ የሚሆኑበትን አቅጣጫ የማስቀመጥና መልክ የማስያዝ ሥራዎች ከወዲሁ እየተሰሩ ነው፡፡ ይሁን እንጂ የዓለምን እንቅስቃሴ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሽባ ያደረገው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ነገሮችን መልክ ለማስያዝ በሚያደርገው እንቅስቃሴ አሁንም ፈተና እየሆነ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ አልሸሸጉም፡፡ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከተጠቀሱት ፈተናዎች በተጨማሪ ሌሎችም እንቅፋቶች ይኖሩበታል:: ከውድድር ጋር በተያያዘ ለኦሊምፒኩ አስፈላጊውን መስፈርት (ሚኒማ) በተለያዩ ስፖርቶች አሟልተው የነበሩ በሺ የሚቆጠሩ አትሌቶች መስፈርታቸው ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ለሚካሄደው ኦሊምፒክ ይስራ አይስራ እርግጠኞች አይደሉም፡፡ በኦሊምፒክ ለመሳተፍ በየትኛውም ስፖርት አንድ አትሌት መስፈርቶችን ማሟላት የግድ ይለዋል፡፡ ከአስራ ስድስት ወር በፊት መስፈርት ያሟላ አትሌት ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ያሟላል ወይም አሁን ያለውን አቋም ይዞ ይቆያል ማለት አይቻልም፡፡ የተራዘመው ኦሊምፒክ ሲቃረብ አትሌቶች ዳግም መስፈርት አሟልተው ይወዳደሩ ማለት ደግሞ ሌላ ጣጣ ይዞ ይመጣል፡፡ ዛሬ መስፈርቱን ያሟላ አትሌት ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ዳግም ላያሟላ ይችላል፡፡ ስለዚህ ይህን ጉዳይ ለማስተካከል ራሱን የቻለ ትልቅ የቤት ሥራ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ይሁን እንጂ የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ኃላፊው ኪት ማክኮኔል አሁን መስፈርቱን ያሟሉ አትሌቶች ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ መስፈርታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ይቆያል ብለዋል፡፡ ይህ በራሱ ግን ኋላ ላይ ጭቅጭቅ አለማስነሳቱን እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡ ከሰላሳ ሦስት ዓለም አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖች ከአስራ አንድ ሺ በላይ አትሌቶች መስፈርቱን አሟልተው ለውድድር እየተዘጋጁ ባሉበት ሁኔታ ኦሊምፒኩ መራዘሙ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን በኦሊምፒክ እግር ኳስ ውድድር የሚሳተፉ የወንድ ተጫዋቾች እድሜ ከሃያ ሦስት እስከ ሃያ አራት መሆን እንዳለበት ይታወቃል፡፡አሁን ኦሊምፒኩ በመራዘሙ በርካታ ተጫዋቾች ከዚህ እድሜ ሊያልፉ መቻላቸው ሌላው ፈተና ይሆናል፡፡ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴም ይህን ጉዳይ መልክ ለማስያዝ ጉዳዩ ከሚመለከተው ፊፋ ጋር በቅርቡ ውይይት ለማድረግ እንዳሰበ ተጠቁሟል፡፡ ኦሊምፒኩን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ለማስተላለፍ የተዋዋለው የአሜሪካን ኩባንያ ኦሊምፒኩ በሚካሄድበት ወቅት ከምንም በላይ የሚጠብቀው የኤንቢኤና ሌሎች ታላላቅ የአሜሪካን ቅርጫት ኳስ ውድድሮች ስለሚኖሩበት የፍላጎትና የጥቅም ግጭቶች ሊፈጠር ይችላል፡፡ ይህ ደግሞ አንዱን ወገን በቢሊዮን ዶላሮች ኪሳራ ላይ ሊጥል ስለሚችል ከባድ ፈተና እንደሚሆን ይታመናል:: በተመሳሳይ ከዚህ ዓመት የተላለፉ በርካቶቹ ዓለም አቀፍ ውድድሮች የሚካሄዱበት መሆኑ ሌላ ጣጣ ይዞ መምጣቱ አይቀሬ ነው፡፡ በነዚህ ወራት ከሚካሄዱ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮች መካከል የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናና የዓለም ውሃ ዋና ቻምፒዮና ዋነኞቹ ቢሆኑም ውድድራቸውን ለመሰረዝ ፍቃደኛነታቸውን መግለፃቸው ይታወቃል፡፡ ይህ አበረታችና ለዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ተስፋ የሰጠ ቢሆንም በነዚህ አካላት መካከል ተጨማሪ የውል ስምምነት እንደሚኖር ይጠበቃል፡፡ ይህ ምናልባትም ሌሎቹ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖችም ለኦሊምፒክ ቅድሚያ እንዲሰጡ ማነሳሳት ቢችልም ወቅቱ በጣም ከፍተኛ ሙቀት የሚኖርበት መሆኑ ለውድድሮች አስቸጋሪ እንደሚሆን ስጋት አሳድሯል:: ምንም ይሁን ምንም ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ የጃፓን መንግሥትን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ እንደሚገቡ ቀደም ሲል ተዘግቧል፡፡ የጃፓኑ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም ገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ ኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል ተናግሯል፡፡ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለዚህ ኪሳራ ስጋት ሰላሳ ሦስቱንም ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን የገባ ቢሆንም በቂ እንደማይሆን ታምኖበታል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ቶማስ ባኽም ኦሊምፒኩ መራዘሙን በገለፁበት ወቅት ከባድ ኪሳራ እንደሚኖር በማመን ሁሉም ባለድርሻ አካላት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል:: ከባዱን መስዋዕትነት ማን እንደሚከፍልና ጫናው በየትኛው ወገን ትከሻ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ግን ዛሬ ላይ ቆሞ በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 28/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "a6817872051fa117ab913c4d9ad9c3f2" }, { "passage": "ቦጋለ አበበ ከትንሿ አርሲ ዞን ተነስተው ከመካከለኛ እስከ ረጅም ርቀት የአትሌቲክስ ውድድሮች ዓለምን ከተቆጣጠሩ በርካታ እንቁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አንዱ ነው። የአትሌቲክስ ሕይወት አነሳሱ ትንሽ ቢሆንም፣ በታላቅ ክብርና ድሎች ታጅቦ ስሙን ከምን ጊዜም ጀግና አትሌቶች ተርታ በወርቅ ቀለም አፅፏል። በትንሽ የውድድር ዘመኑ ትልልቅ ስፖርታዊ ገድሎችን በመፈፀምም ለረጅም የውድድር ዓመታት በስፖርቱ ከቆዩ ጀግና አትሌቶች ያልተናነሰ ታሪክ ሰርቷል። የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና የማራቶን አሸናፊው ጀግና አትሌት ገዛኸኝ አበራ። ገና በአፍላ እድሜው በሬድዮ አንድ የስፖርት ዘገባ ሰምቶ ወደ አትሌቲክሱ ለመግባት የተነሳሳበት አጋጣሚ ከበርካታ ውጣ ውረዶች በኋላ ትልቅ ታሪክ ሰሪ እንዳደረገው ይናገራል። ገዛኸኝ የወደፊት የሕይወቱ እጣፋንታን ለመወሰን ‹አንድ ፈረንሳዊ ሃያ አንድ ኪሎ ሜትርን በ1፡02 ደቂቃ አጠናቆ መኪና ተሸለመ› በሚል በሬድዮ የሰማው የስፖርት ዘገባ እሱ በወቅቱ በደርሶ መልስ ሃያ አምስት ኪሎ ሜትሮችን እየተጓዘ ወደ ትምህርት ገበታው ከሚመላለስበት ሁኔታ ጋር እንዲያሰላ ጥያቄ ፈጠረበት። ‹‹ይሄ አትሌት ሃያ አንድ ኪሎ ሜትርን በዚህ ሰዓት ካጠናቀቀ እኔ ስንት ይፈጅብኛል›› ብሎም ራሱን ጠየቀ። ወደ ስፖርቱ ለመግባት የተነሳሳውም በዚህ አጋጣሚ እንደነበር በርካታ ዓመታትን ወደ ኋላ ተመልሶ ዛሬ ላይ ያስታውሳል። ገዛኸኝ በትንሽ አጋጣሚ ወደ ስፖርቱ ብቅ ቢልም እንዳብዛኞቹ የአገራችን አትሌቶች በርካታ የሕይወት ውጣውረዶችን ለማሰለፍ ተገዷል። በተለይም ከውጤት ማጣት ጋር በተያያዘ ከክለቡ እስከ መቀነስ የደረሰ ፈተና ገጥሞት እንደነበር ያስታውሳል። ዓለም ዛሬ ላይ ገዛኸኝን የሚያውቀውና የሚያስታውሰው በማራቶን ተወዳዳሪነቱ ነው። በእርግጥ ገዛኸኝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለትልቅ ስኬት የበቃው በማራቶን ነው። በሌሎች ርቀቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ውድድሮች ሲያደርግም የሚያውቀው የለም። በማራቶን የዓለምን ሕዝብ ተዋወቀ፤ በማራቶን ከስፖርቱ ጋር ተለያየ። ይህም ‹‹የማራቶን ሰው!›› አሰኝቶታል። ይሁን እንጂ ገዛኸኝ ዓለም ሳያውቀው ከማራቶን ውጪ በአገር ውስጥ ውድድሮች እንደ አስርና አምስት ሺ ሜትር ያሉ ውድድሮች ያደርግ ነበር። ታሪክ ይሰራበት ዘንድ መክሊቱን ያገኘው ግን ፈተናዎች በተጋረጡበት በአንድ አጋጣሚ ነበር። ገዛኸኝ በሚወዳደርባቸው ርቀቶች ውጤት እየራቀው ክለቡ በዚህ ምክንያት ሊያሰናብተው ሁለት ሳምንታት በቀሩት ጊዜ ከጉዳት ጋር እየታገለ ባህርዳር ላይ አንድ ውድድር አደረገ። በዚህ ውድድር ላይ ውጤት ካላስመዘገበ የፈራው አደጋ አይቀሬ ነው። ሆኖም በለስ ቀንቶት በዚህ ውድድር ሦስተኛ ሆኖ አጠናቀቀ። ይህም ከክለቡ ጋር የሚኖረውን እህል ውሃ እንዲያስቀጥል ከማድረጉ ባሻገር ብሔራዊ ቡድን በሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች አይን እንዲገባ አስቻለው። የወደፊት ዓለም አቀፍ ውድድሮች በር ተከፍቶለትም እኤአ 1999 ሎሳንጀለስ ማራቶን ላይ ተሳታፊ ሆኖ ሦስት ኬንያውያን አትሌቶችን ተከትሎ በመግባት አራተኛ ሆኖ አጠናቀቀ። ይህም እኤአ ለ1999 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና አገሩን ወክሎ እንዲወዳደር አደረገው። ሆኖም በዚያ የዓለም ቻምፒዮና አስራ አንደኛ ሆኖ በማጠናቀቁ ጥሩ የማይባል ውጤት አስመዘገበ። በዚህ ውጤት ተስፋ ያልቆረጠው ገዛኸኝ በተመሳሳይ የውድድር ዓመት በፎኮካ ማራቶን ተሳትፎ የመጀመሪያ ዓለም አቀፍ ድሉን ለማጣጣም ያገደው አልነበረም። እኤአ 2001 ና 2002 በጃፓን ምድር የሚካሄደውን የፎኮካ ማራቶን ማሸነፍ ችሏል። ከዚያም በፊት እኤአ 2000 ላይ በቦስተን ማራቶን ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል። ገዛኸኝ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ትልቅ ቦታ በሚሰጠው የሲድኒ\n2000 ኦሊምፒክም በማራቶን የማይረሳ ድል አስመዘገበ። ይህም በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ታሪክ ከማሞ ወልዴ ድል ከሰላሳ ሁለት ዓመት በኋላ በማራቶን የጀገነ አትሌት አድርጎታል። እኤአ 1932 ሎሳንጀለስ ኦሊምፒክ ከጁአን ካርሎስ ዛባላ ቀጥሎ በሃያ ሁለት ዓመቱ ወይም በትንሽ እድሜው የኦሊምፒክ ማራቶንን በማሸነፍ ሌላ የታሪክ ካባ ደርቧል። በአስራ አንድ ወራት ልዩነትም እኤአ 2001 ኤድመንተን የዓለም ቻምፒዮና ላይ በማሸነፍ ብቸኛው የዓለማችን አትሌት ለመሆን በቅቷል። እኤአ 2003 ላይ ታላቁን የለንደን ማራቶን በ2፡07፡56 ማሸነፍ የቻለው ገዛኸኝ በተመሳሳይ ዓመት ለዓለም ቻምፒዮና አገሩን ወክሎ እንዲወዳደር እድል ቢያገኝም በጉዳት ምክንያት ሳይሳተፍ ቀርቷል። ከዓመት በኋላ ባለቤቱ እልፍነሽ ዓለሙ በማራቶን አራተኛ ደረጃን ይዛ ባጠናቀቀችበት የ2004 አቴንስ ኦሊምፒክ ገዛኸኝ ኢትዮጵያን የመወከል እድል አግኝቶ ያጋጠመው ተደጋጋሚ ጉዳት ታሪክ እንዳይደግም እንቅፋት ሆኖበታል። በተደጋጋሚ የሚገጥመው ጉዳት ከዚያ በኋላ ወደ ውድድር እንዳይመለስም አድርጎታል። ገዛኸኝ ውድድር ላይ በቆየባቸው ጥቂት ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ በማራቶን ጀምሮ በማራቶን ቢሰናበትም ዘመን የማይሽረው ታሪክ አኑሯል። ብዙ የስፖርት ቤተሰቦች ገዛኸኝ ረጅም ዓመት በውድድር ላይ ቢቆይ ብዙ ታሪኮችን ይሰራ እንደነበር ያምናሉ። እሱ ግን በዚህ ብዙም አይቆጭም። ‹‹እኔ ሁለት ክብረወሰኖች አሉኝ፣ አንዱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ውጤታማነት መጥቶ ኦሊምፒክ ላይ ማሸነፍ ሲሆን ሌላኛው በአጭር ጊዜ ውድድር በማቆም ነው›› በማለት ይቀልዳል። ለብሔራዊ ቡድን የተመረጠው በማራቶን ነው፣ ውጤታማ የሆነውም በዚሁ ርቀት ነው። ሆኖም ውጤታማነቱን በቅጡ እንኳን ደጋግሞ ሳያጣጥም ጉዳት ከስፖርቱ እንዳራቀው ይናገራል። ገዛኸኝ ሌላው ቢቀር በማራቶን የዓለምን ክብረወሰን ማሻሻል በሚችልበት ወቅት በጉዳት ከውድድር ርቆ መቅረቱ የሚያስቆጫቸው ጥቂት አይደሉም። እሱ ግን ከክብረወሰን በበለጠ በርቀቱ የሰራው ታሪክ ትልቅ እንደሆነ ያምናል። አንድ አትሌት ዛሬ ተነስቶ የዓለም ክብረወሰን ቢያስመዘግብ ከዓመት በኋላ ወይም ከዚያ ባነሰ ጊዜ ሌላ አትሌት ሊሰብረው ይችላል። ክብረወሰኖች በየጊዜው ይሻሻላሉ፣ ገዛኸኝን የሚያሳስበው ግን ኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና ላይ ውጤት አምጥቶ የአገርን ስም በክብር ማስጠራት ነው። በእርግጥ ክብረወሰን ማስመዝገብ ቀላል ነገር ነው የሚል እምነት የለውም። በመገናኛ ብዙሃን ከኦሊምፒክና ከዓለም ቻምፒዮንነት በላይ ትልቅ ዋጋ ሊሰጠው እንደማይገባ ግን እምነቱ ነው። አንድ አትሌት ክብረወሰን ሲያሻሽል ገንዘብ ያገኛል፣ በገንዘቡም አገርና ሕዝብን ሊጠቅም እንደሚችል ለገዛኸኝ አይጠፋውም፣ ያም ሆኖ ለኦሊምፒክ አሸናፊ የሚሰጠው ቦታ ይበልጥበታል። በተለይም አሁን አሁን ክብረወሰን ለማሻሻል አንድ አትሌት በአሯሯጥና በቴክኖሎጂ ታግዞ ከራሱና ከሰዓት ጋር በሚፎካከርበት ዘመን በኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና ከዓለም አትሌቶች ጋር ተፎካክሮ ለውጤት የሚበቃ አትሌት ለየቅል እንደሆኑም ያስባል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቅርቡ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በስራ አስፈፃሚነት ስፖርቱን ለማገልገል ወደ ፊት የመጣው ገዛኸኝ፣ ፌዴሬሽኑን በምክትል ፕሬዚዳንትነትና የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢነት ለማገልገል እድል አግኝቷል። በርካታ የስፖርቱ ዓለም ሰዎች ከውድድር ዘመናቸው በኋላ ወደ አሰልጣኝነት ሲመጡ ቢስተዋልም ገዛኸኝ ወደ ኢንቨስትመንቱ መሰማራትን መርጧል። ወደ አሰልጣኝነት እንዳይመጣም ሁኔታዎች ተስፋ እንዳስቆረጡት ይናገራል። በተለይም እሱ ወደ አሰልጣኝነት ለመምጣት እድሉ በነበረው ወቅት በዓለም ላይ የስፖርቱ አሰልጣኝነትም ይሁን አትሌቱ በሽግግር ላይ የነበረበትና ሁኔታዎች እየተለዋወጡ የመጡበት መሆኑን ያስታውሳል። ‹‹እኔ የመርህ ሰው ነኝ፣ ለአንድ ሰው ትዕዛዝ ስሰጥ በቅንነት መንፈስ ነው፣ ያዘዝኩት ነገር ከእኔ በተሻለ እንዲፈፀም እፈልጋለሁ፣ በጣም እልኸኛ ነኝ፣ ይህን ሳስብ ከአሰልጣኝነት ጋር በተያያዘ ነገሮች እየተለወጡ ሲመጡ አስተውያለሁ›› ይላል። በተለይም አንድ አሰልጣኝ ከስር ጀምሮ አትሌቱን አሳድጎ ለውጤት በሚበቃበት ወቅት በሌሎች አሰልጣኞችና ማኔጀሮች የሚነጠቅበት ሁኔታ አሰልጣኝ ለመሆን ተስፋ የሚያስቆርጥ እንደሆነ ይናገራል። የፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ሆኖም ይህን ጉዳይ ለማስተካከል ከሌሎቹ ጋር ጥረት እንደሚያደርግ እግረመንገዱን ይጠቁማል። በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ታሪክ ከጀግኖቹ አበበ ቢቂላና ማሞ ወልዴ ቀጥሎ ገዛኸኝ በኦሊምፒክ ማራቶን ሲያሸንፍ ሦስተኛው አትሌት ነው። ከእሱ በኋላ ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ የማራቶን አሸናፊ ካገኘች ሁለት አስርት ዓመታት ተቆጥረዋል። ከማሞ ወልዴ ድል በኋላ ኢትዮጵያ ገዛኸኝን እስክታገኝ ሰላሳ ሁለት ዓመታት ተቆጥረዋል። አሁንም የገዛኸኝን ድል የሚደግም አትሌት እስኪመጣ ሰላሳ ሁለት ዓመት መጠበቅ እንደሌለበት ገዛኸኝ በቁጭት ይናገራል። ‹‹እኔ ባሸነፍኩኝ በአራት ዓመቱ ሌላ አትሌት ቢያሸንፍ ምኞቴ ነው›› የሚለው ገዛኸኝ፣ ሁል ጊዜ ከአበበና ማሞ ቀጥሎ ሦስተኛው አትሌት መባል አይፈልግም። ከእሱ ቀጥሎ አራተኛው፣ አምስተኛው ወዘተ አትሌት የሚመጣበትን ጊዜ ይናፍቃል። ‹‹ትውልድ ቅብብሎሽ ነው፣ ይብዛም ይነስም እሱ የሰራው ታሪክ ሕያው ሆኖ ይኖራል፣ የትውልድ ቅብብሎሹ እንደ አገር መቀጠል አለበት፣ የኦሊምፒክ የማራቶን ድል አንድ ቀን ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳል›› ብሎ በማመንም በፌዴሬሽን አመራርነት ዘመኑ ልምድና እውቀቱን አጣምሮ ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ እየሰራ ነው። ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ ታሪክ የገዛኸኝን የማራቶን ድል ጨምሮ አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን የሰበሰበችበት ወርቃማው የሲድኒ 2000 ትውልድ ብዙ ስራ ቢጠይቅም አንድ ቀን እንደሚደገም ገዛኸኝ ብርቱ እምነት አለው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በስፖርቱም በአትሌቱም ዘንድ ቴክኖሎጂ ያመጣቸው ችግሮች የአትሌቱን ስነልቦናና መንፈስ በመጠኑም ቢሆን ወደ ኋላ ሊጎትቱት እንደሚችሉ ቢያምንም በቁርጠኝነት ከተሰራ ችግሮችን ተሻግሮ ውጤት ማምጣት የሚቻልበት እድል እንዳለ ያስረዳል። ለዚህም ለውጥ የሚጀምረው ከራስ ነውና ሁሉም ራሱን አሸንፎ ለትውልድ አንድ አሻራ ጥሎ ማለፍ እንዳለበት ከራሱ ተሞክሮ ተነስቶ ምሳሌ ያስቀምጣል። ‹‹እኔ ወደ ስፖርቱ ስመጣ አገሬን አስጠራለሁ ብየ አይደለም፣ አትሌቲክስ እንጀራዬ ይሆናል ብዬ እንጂ፣ እኔ ራሴን ሳሸንፍ ከራሴ አልፌ ለቤተሰብ እተርፋለሁ፣ ከዚያም ለአገር›› በማለትም ምክሩን ይለግሳል። ገዛኸኝ በሕይወት ዘመኑ ይሄን ማድረግ ሲኖርብኝ አላደረኩም፣ ይሄን ማሳካት ሲኖርብኝ አላሳካሁም ብሎ ባለፈ ነገር የሚፀፀት አይነት ሰው አይደለም። ለዚህም አንድ የሕይወት ፍልስፍና ወይም እምነት አለው። ‹‹ ይብዛም ይነስም ላገኘሁት ስኬትና እውቅና ገና በእናቴ ማህፀን እንዳለሁ ፈጣሪ ያውቅ ነበር ብዬ አምናለሁ፣ ይሄን ካመንኩኝ ያደረኩትን ነገር አለማድረግ አልችልም ማለት ነው፣ ያላደረኩትን ነገር ላድርግ ብልም ማድረግ አልችልም ማለት ነው፣ ስለዚህ በሕይወቴ አላሳካሁም ብዬ የምፀፀትበት ነገር የለም›› ይላል። እኤአ ከ2003 በኋላ ከውድድር ከራቀ ወዲህ በተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተሰማርቶ ከባለቤቱ እልፍነሽ ዓለሙ ጋር ለበርካታ ዜጎች የሰራ እድል በመፍጠር አገሩን ዳግም እያገለገለ የሚገኘው ገዛኸኝ፣ ከስፖርቱ ውጪ ያለው ሕይወቱ ብዙም ሲነገር አይታይም። ብዙዎችም የሚያውቁት ሐዋሳ ከተማ በባለቤቱና በእሱ ስም ያለውን የሆቴልና ሪዞርት ኢንቨስትመንት ነው። ገዛኸኝ በቅርቡ በቢሾፍቱ ሐይቅ ዳርቻ ሃያ ሺ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሌላ ሆቴልና ሪዞርት ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ይገኛል። በአገር ውስጥም በውጪ አገርም ከባለቤቱ እልፍነሽ ጋር በመሆን ሌሎች ንግድ ስራዎች ላይ ተሰማርቶ ይገኛል።", "passage_id": "3a39c256301b1895054308d6f1f917ab" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳ በአትሌቲክስ ስፖርት እንደ ሌሎች የስፖርት ዓይነቶች በዓለም ላይ የበላይነቱን መጎናጸፍ ያልቻሉት ምዕራባውያኑ ካለሙት ለመድረስ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም። በተለይ በመካከለኛና ረጅም ርቀት አትሌቲክስ ስፖርቶች ተወዳዳሪ መሆን አለመቻላቸውና ውጤታማነቱ በአፍሪካውያን መያዙ ሁሌም ያሳስባቸዋል። በዚህም ምክንያት ስኬታማ ሊያደርጓቸው የሚችሉ አማራጮችን ከመሞከር ወደ ኋላ አይሉም። የስፖርት አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቃሚነት ከዚህ የመነጨ ሲሆን፤ እንደቀደሙት ዓመታት የተጠቃሚነት ፈተናውን በቀላሉ ማለፍ አለመቻላቸውን ተከትሎ ሌላ ዘዴ መፈለጋቸው አልቀረም። ይኸውም ፍጥነትን ለመጨመር የሚረዱ ጫማዎችን ወደ ገበያው በማስገባት ነው። ነገር ግን ይህ የቴክኖሎጂ ውጤትም ‹‹ጨዋታ ቀያሪ›› ሊባል የሚችልና ከአትሌቶች ተፈጥሯዊ አቅም በላይ የሆነ ተጨማሪ ፍጥነት ስለሚሰጠው በብዙዎች ተቃውሞ ገጥሞታል። ከስፖርቱ ቤተሰብም ባለፈ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስፖርቱን የሚመሩት ማህበራትም የነገሩን አሳሳቢነት በመገንዘብ አትሌቶች ይህንን መሰል ጫማ ከግል ውድድር ውጪ በኦሊምፒክና መሰል ውድድሮች ላይ እንዳይጫሙት ሲከለክሉ ቆይተዋል። ዘጋርዲያን ከሰሞኑ እንዳስነበበው ከሆነ ደግሞ የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ በዚህ ጉዳይ ላይ መለሳለስ ያሳዩበትን አስተያየት ሰጥተዋል። ናይኪ የተባለው የስፖርት ትጥቆች አምራች ድርጅት በቅርቡ አንድ የመሮጫ ጫማ ዓይነት ለዓለም አስተዋውቋል። ይህንን ለጎዳና ሩጫዎች የተመረተ ጫማም በመጀመሪያ በማራቶን ያስሞከረ ሲሆን፤ ኬንያዊው የዓለም ክብረወሰን ባለቤት ኢሉድ ኪፕቾጌ ርቀቱን በዓለም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሁለት ሰዓት በታች ፈጽሟል። ይህንንም ተከትሎ በአትሌቶች ዘንድ ተፈላጊነቱ ሲበረታ በተፈጥሯዊ ስፖርት በሚያምኑ በስፖርት ባለሙያዎችና የአትሌቲክስ ወዳጆች ግን ተቃውሞ ደርሶበታል። በእርግ ጥ በዚህ\nጫማ ከተካሄዱ ውድድሮችአብዛኛዎቹ እንደየርቀቱ ፈጣን ሰዓት የተመዘገበባቸውና ክብረወሰንም የተሻሻለባቸው ናቸው። ለአብነት ያህልም በቅርቡ፤ በወንድና በሴት የ10ሺ እና የ5ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገቡት አትሌቶች ጆሹዋ ቼፕቴጊ እና ለተሰነበት ግደይ የናይኪ ምርት በሆነው ‹‹ዙምኤክስ ድራጎንፍላይ›› የተባለ ጫማ ነበር የሮጡት። በተመሳሳይ ሞሃመድ ፋራህ እና ሲፋን ሃሰንም የአንድ ሰዓት ክብረወሰኑን የግላቸው ማድረግ የቻሉት በዚሁ የመሮጫ ጫማ ነው። ይህም ትጥቅ አምራቹን ድርጅት በሥራው እርግጠኛ ሲያደርገው በአትሌቶች ደግሞ ፍላጎቱን አንሮታል። ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው የዓለም አትሌቲክስ ባለፈው ዓመት በጫማው ላይ ስጋት ያለበት የሚያስመስለውን ህግ፤ ኦሊምፒክን ጨምሮ በትልልቅ የውድድር መድረኮች ላይ ሶላቸው ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ የሆኑ የመሮጫ ጫማዎችን ማድረግ እንደማይቻል ይፋ አድርጎ ነበር። በቅርቡ ደግሞ ጫማው በኦሊምፒክ ላይም ፈቃድ ሊያገኝ ይችላል የሚለው ሃሳብ መሰማቱን ተከትሎ ብዙዎችን ሲያነጋግር ቆይቷል። አዲሱን የፈረንጆች ዓመት መግባት ተከትሎም ስለ ጫማው አስተያየት የሰጡት የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት፤ በቅርቡ የተሻሻሉ የዓለም ክብረወሰኖች በጫማው እገዛ ነው የሚለው ትክክል አመሆኑን አንጸባርቀዋል። ስለ መሮጫ ጫማው የተጋነነ ስሜት እንደሌላቸው የሚገልጹት ፕሬዚዳንቱ ‹‹እአአ በ2ሺ አጋማሽ የረጅም ርቀቶች ንግስናውን የተቆጣጠረው አዲዳስ ነበር። ይኸው ነገር አሁንም ተመልሶ ታየ፤ ፋብሪካዎቹ ግን አሁንም አዳዲስ የፈጠራ ምርቶችን ወደ ገበያ ከማቅረብ ወደኋላ አላሉም። በመሆኑም ህጎችን መከለስ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል›› ብለዋል። የክብረወሰን ባለቤት የሆኑትን\nአትሌቶች ብቃት በጫማው\nመለካት እና ጫማው\nእገዛ አድርጎላቸዋል የሚለው\nሃሳብም ስፖርቱን ዝቅ\nአድርጎ ከመመልከት የመጣ\nእንደሆነም ጠቁመዋል። ነገሮችን\nያማከለ ዳኝነትና የፈጠራ\nሥራዎችን ማፈን አስፈላጊ\nአለመሆኑን ነው ያስታወቁት።\nይኸው የፕሬዚዳንቱ ንግግርም\nጫማው ኦሊምፒክ ላይም\nፈቃድ ሊያገኝ ይችላል\nየሚለውን ግምት የሚያጠናክር\nሆኗል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 27/2013", "passage_id": "06c472a1677a1a8052993bf69801b58a" }, { "passage": "ዓለምን እያሳሰበ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሳቢያ መካሄድ አለመካሄዱ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አምስት ወራት የቀሩት ቢሆንም በርካታ የዓለማችን አገራት በተለያዩ ስፖርቶች የሚያደርጉትን ዝግጅት አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ኢትዮጵያም በዚህ ታላቅ የስፖርት መድረክ በተለይም በአትሌቲክስ ረጅምና መካከለኛ ርቀቶች ውጤታማ እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በቀድሞው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አባዱላ ገመዳ የሚመራ ብሔራዊ የዝግጅት ኮሚቴ በማዋቀር የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ሰንብቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውጤት በሚጠበቅበት የአትሌቲክስ ስፖርት ኢትዮጵያን እንዲወክሉ\nየተመረጡ አትሌቶች ከመጋቢት ሦስት ጀምሮ ወደ ሆቴል ገብተው ዝግጅት እንዲጀምሩ ውሳኔ ላይ መድረሱን ያሳወቀ ሲሆን፣ አትሌቶችና\nአሰልጣኞች ከትናንት ጀምሮ በኦሊምፒክ ኮሚቴ ፅሕፈት ቤት በአካል በመገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሁለት ሳምንት በፊት በኦሊምፒኩ ኢትዮጵያን የሚወክሉ\nአትሌቶችና አሰልጣኞችን መልምሎ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በመካከለኛ ርቀት፣ ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል፣ ረጅም ርቀት፣ ማራቶንና\nርምጃ ውድድሮች አሰልጣኞችና አትሌቶች መመረጣቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት\nበመካከለኛ ርቀት አሰልጣኝ ብርሃኑ መኮንን፣ ሃብታሙ ግርማ፣ ኢሳ ሽቦ እና ጉዲሳ ታሱ በአሰልጣኝነት ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም\nኃይለማሪያም እና ስንታየሁ ካሳሁን ደግሞ በተጠባባቂነት ተይዘዋል፡፡ በ3ሺ ሜትር መሰናክል ደግሞ አሰልጣኝ ተሾመ ከበደ እና ዶክተር\nብዙአየሁ ታረቀኝ ሲመረጡ አሰልጣን ከፍያለው አለሙ ተጠባባቂ ሆነዋል፡፡ አገሪቷ በኦሊምፒክ\nመድረክ በተለይ ውጤታማ በሆነችባቸው የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር ርቀቶችም አራት አሰልጣኞች ተመራጭ ሆነዋል፡፡ አሰልጣኝ ሁሴን ሸቦ፣\nቶሌራ ዲንቃ፣ ንጋቱ ወርቁ እና ኃይሌ እያሱ ሲመረጡ፤ አሰልጣኝ ተፈሪ መኮንን እና በሪሁን ተስፋይ ደግሞ የተጠባባቂነት ስፍራን\nይዘዋል፡፡ በረጅሙ የአትሌቲክስ ውድድር ማራቶን በማናጀር አሰልጣኝነት ስኬታማ የሆኑት አሰልጣኝ ሃጂ አደሎ ከሌላው ስኬታማ አሰልጣኝ\nገመዶ ደደፎ ጋር በመሆን የርቀቱን እንዲመሩም ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኝ ጌታነህ ተሰማ እና ይረፉ ብርሃኑ ደግሞ ተጠባባቂ ሆነው ተይዘዋል፡፡\nየእርምጃ ቡድኑም በሻለቃ ባየ አሰፋ አሰልጣኝነት የሚያመራ ይሆናል፡፡ ውጤት በሚጠበቅበትና\nታሪካዊ ሊሆን እንደሚችል በሚታሰበው የወንዶች ማራቶን ውድድር የ5ና 10ሺ ሜትር የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑና የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ\nአትሌት ቀነኒሳ በቀለ ባለፈው መስከረም በበርሊን ማራቶን ባስመዘገበው ፈጣን ሰዓት መሰረት በዋናነት መመረጡ የሚታወስ ሲሆን ማራቶንን\nጨምሮ በሌሎች ርቀትም ጠንካራ አትሌቶች በቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን ለመወከል ወደ ዝግጅት ይገባሉ፡፡ ከነዚህም መካከል በዶሃው\nቻምፒዮና ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው አትሌት ሞስነት ገረመው 2፡02፡55 የሆነ ሰዓት ባለፈው ለንደን ማራቶን ላይ በማስመዝገቡ በማራቶን\nቡድኑ ውስጥ በሦስተኛ ደረጃ ተመራጭ ሆኗል፡፡ ብርሃኑ ለገሰ በ2፡02፡48 በሁለተኛነት ሲመረጥ የዓለም ሻምፒዮኑ አትሌት ሌሊሳ\nዴሲሳ ከሌሎች አትሌቶች አኳያ ያለው የቅርብ ጊዜ ፈጣን ሰዓት በቡድኑ ሊያካትተው እንደማይችል ይፋ ከተደረገው የእጩዎቹ ዝርዝር\nመረዳት ተችሏል፡፡ በሴቶች ማራቶን የዱባይ ማራቶን አሸናፊዋ ወርቅነሽ ደገፋ 2፡17፡41 ሰዓት በመያዝ በቀዳሚነት ስሟ ሲቀመጥ\nሮዛ ደረጄ 2፡18፡30ና በ2፡18፡34 ሰዓት ሩቲ አጋ በቀዳሚነት ታጭተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በሚጠበቁበት\nየአስር ሺ ሜትር ውድድር የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ አሸናፊው ዮሚፍ ቀጄልቻ 26፡49፡34 በሆነ ሰዓት ሲመረጥ አንዱአምላክ\nበልሁ 26፡53፡15ና በ26፡54፡34 ጀማል ይመር በቀዳሚነት ተመርጠዋል፡፡ በሴቶች የኦሊምፒክ ቻምፒዮኗ አልማዝ አያና ከዓመት\nበላይ በጉዳት ላይ የቆየች ቢሆንም ቀዳሚዋ ተመራጭ መሆን ችላለች፡፡የዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ባለቤቷ ለተሰንበት ግደይና ነፃነት\nጉደታም ከቀዳሚዎቹ እጩዎች መካከል ተካተዋል፡፡ በወንዶች አምስት\nሺ ሜትር በዶሃው የዓለም ሻምፒዮና የወርቅና የብር ሜዳሊያ ያጠለቁት ሙክታር ኢድሪስና ሰለሞን ባረጋ እንዲሁም ሃጎስ ገብረህይወትና\nጥላሁን ሃይሌ በቀዳሚነት ሊመረጡ ችለዋል፡፡ በሴቶች ደግሞ ጸሐይ ገመቹ፣ ሐዊ ፈይሳና ፋንቱ ወርቁ ባስመዘገቡት ሰዓት መሰረት ሊመረጡ\nችለዋል፡፡ኢትዮጵያ በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ከአትሌቲክስ ውድድሮች በተጨማሪ በታሪክ\nለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ተሳታፊ መሆኗን ከሁለት ሳምንት በፊት ማረጋገጥ ችላለች፡፡ በሞሮኮ ራባት ተካሂዶ በነበረው\nየወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት የኦሊምፒክ ማጣሪያ ውድድር ማስተር ሰለሞን ቱፋ በኦሎምፒክ እንደሚወዳደር ማረጋገጡ አይዘነጋም፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 28/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "0144ad88e4be9c873dc8c3c50637e0f6" } ]
1b85a28f1c8b43de53d12014a7757109
e91a0bae5984a76af014e9c4a6097934
የሦስት ታላላቅ ክለቦች አለቃው መጨረሻ
ዓለም በኮሮና ቫይረስ ስርጭት እየተሸበረች በምትገኝበት በዚህ ጊዜ የስፖርቱ ዓለም ተቆልፎበት ይገኛል። በቫይረሱ ሳቢያ የስፖርቱ ዓለም ሰዎች ከሚወዱት መድረክ እንዲቆጠቡ ከመገደዳቸው በተጨማሪ የቫይረሱ ሰለባ ከመሆን ባሻገር ሕይወታቸውን ያጡም አልጠፉም። የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ዓለም ሌላ የጤና ፈተናዎች የሌሉባት እስኪመስል ድረስ ትኩረት ሁሉ ወደ አንድ አቅጣጫ አዘንብሏል። ከስፖርቱ ዓለም ሰዎች ማን በቫይረሱ ተያዘ? ማንስ ሕይወቱ አለፈ? በሚል የስፖርት ቤተሰቡ ትኩረት ወደ አንድ አቅጣጫ በተጓዘበት ወቅት የስፔን ሦስት ታላላቅ ክለቦችን በማሰልጠን ብቸኛው የሆነው ራዶሚር አንቲች ባለፈው ሰኞ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። የስፔን ታላላቅ ክለቦች የሆኑት ሪያል ማድሪድ፣ ባርሴሎናና አትሌቲኮ ማድሪድ ብቸኛ አሰልጣኝ የሆነው ሰርቢያዊው አንቲች በሰባ አንድ ዓመቱ በማድሪድ ከተማ ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል። ታሪካዊው አሰልጣኝ ስፔንን እያመሳት በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሕይወቱ እንዳለፈ በርካቶች ግምታቸውን ቢያስቀምጡም ለሞት የበቃው ላለፉት ዓመታት ሲያሰቃየው በቆየው ሌላ ሕመም ምክንያት እንደሆነ ተዘግቧል። በሰርቢያ ዛይቲስ ከተማ የተወለደው አንቲች እንደ በርካቶቹ የእግር ኳስ አሰልጣኞች በተጫዋችነት አሳልፏል። የተጫዋችነት ዘመኑ የሚጀምረውም በስሎቦዳ ዩዚስ ክለብ ሲሆን በርካታ የውድድር ዓመታትን በቤልግሬዱ ፓርቲዛን ክለብ እየተጫወተ አሳልፏል። ከዚህ ክለብ ጋርም እ.ኤ.አ በ1975/76 የውድድር ዓመት የዩጎዝላቪያ ሊግ ዋንጫን ማሳካት ችሏል። ወደ ቱርኩ ክለብ ፊነርባቼ በማቅናትም የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ወደ ሪያል ዛራጎዛ አምርቶም ሁለት የውድድር ዓመታትን አሳልፏል። እ.ኤ.አ በ1980 ወደ እንግሊዙ ክለብ ሉተን ታውን አቅንቶም ከአራት የውድድር ዓመታት ቆይታ በኋላ ጫማውን ሰቅሏል። አንቲች ጫማውን ከሰቀለ ወዲህ የአሰልጣኝነት ሕይወቱን የጀመረው በአገሩና ተጫውቶ ባለፈበት የቤልግሬዱ ክለብ ፓርቲዛን ሲሆን በክለቡ ቆይታው ሁለት የቻምፒዮንሺፕ ዋንጫዎችን ማንሳት ችሏል። ከዚያም እ.ኤ.አ በ1988 በተጫዋችነት ወዳሳለፈበት ዛራጎዛ ክለብ አምርቶ ክለቡን የአውሮፓ ካፕ ተሳታፊ ማድረግ ችሏል። እ.ኤ.አ በ1990/91 የውድድር ዓመት አልፍሬዶ ዲ ስቲፋኖን በመተካት የታላቁ ክለብ ሪያል ማድሪድ አሰልጣኝ ለመሆን በቅቷል። ይሁን እንጂ ከታላቁ ክለብ ጋር ውጤታማ ጊዜን ባለማሳለፉ ቆይታው አጭር ነበር። ከሪያል ማድሪድ ያልተሳካ የአሰልጣኝነት ዘመን አጭር ቆይታ በኋላ አንቲች ወደ ሪያል ኦቪዶ በማቅናት ለሁለት የውድድር ዓመታት ስኬቶችን አስመዝግቧል። ይህም ስኬቱ ወደ ታላቁ ክለብ አትሌቲኮ ማድሪድ ዋና አሰልጣኝነት በር የከፈተለት ሲሆን ገና በመጀመሪያ የውድድር ዓመቱ እ.ኤ.አ 1995/96 የውድድር ዓመት የሊጉን ዋንጫና የኮፓዲላሬ ስኬቶችን መጎናፀፍ ችሏል። ይህም በክለቡ ታሪክ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ሲሆን ዛሬም ድረስ የሚዘከር ነው። አንቲች በአትሌቲኮ ማድሪድ ያሳለፋቸው አምስት ዓመታትም ክለቡ ከምንም ተነስቶ አሁን ላይ ከስፔን ታላላቅ ክለቦች አንዱ ለመሆኑ መሰረት የያዘበት ሆኖ ይነገራል። ከአትሌቲኮ ማድሪድ ስኬታማ አምስት ዓመታት በኋላ ወደ ሪያል ኦቪዶ የተመለሰው አንቲች በውድድር ዓመቱ ክለቡ ከሊጉ በመውረዱ ብዙም ሳይቆይ እ.ኤ.አ 2003 ላይ ወደ ታላቁ የካታላን ክለብ ባርሴሎና አሰልጣኝ ሊውስ ቫንሃልን ተክቶ ሊፈርም ችሏል። በወቅቱ ባርሴሎና ወራጅ ቀጠና ከነበረው ክለብ በሦስት ነጥብ ከፍብሎ የመውረድ ሥጋት የተጋረጠበት ቢሆንም በአንቲች አሰልጣኝነት ስድስተኛ ደረጃን ይዞ ሊያጠናቅቅ ችሏል። ይህም በአውሮፓ ካፕ ተሳታፊነቱን አረጋግጦለታል። እንደ አጋጣሚ ሆኖ በቀጣይ የውድድር ዓመት ክለቡን ለመምራት የተመረጡት አዲሱ ፕሬዚዳንት ሁዋን ላፖርታ አንቲች በካታላኑ ሃያል ክለብ አሰልጣኝነት እንዲቀጥል አልፈለጉም። ይህም ወደ ሴልታቪጎ እንዲያመራ አድርጎታል። እዚያም ግን ቆይታው አጭር ነበር። እ.ኤ.አ 2008 ላይ የሰርቢያን ብሔራዊ ቡድን ወደ 2010 የደቡብ አፍሪካ ዓለም ዋንጫ ለማሳለፍ ሃላፊነቱን የወሰደው አንቲች በማጣሪያው ሊሳካለት አልቻለም። ከአገሩ ብሔራዊ ቡድን ጋር የነበረው ቆይታም በዚሁ በአጭር ተቀጭቷል። ከዚያ በኋላ ግን ለአራት ዓመታት እ.ኤ.አ እስከ 2016 ድረስ በቻይና ሊግ በርካታ ክለቦችን በአሰልጣኝነት መርቷል። ሦስቱን ታላላቅ የስፔን ክለቦች በአሰልጣኝነት በመምራት ብቸኛው ሰው የነበረው አንቲች ባለፈው ሰኞች ለረጅም ጊዜ በቆየበት ሕመም ሕይወቱ ካለፈ በኋላ የስፖርት ቤተሰቡ በተለያዩ መንገዶች ሐዘኑን እየገለፀ ይገኛል። ከነዚህ መካከል የአትሌቲኮ ማድሪዱ ፕሬዚዳንት ኪኮ ‹‹የአትሌቲኮ ማድሪድን ድንቅ መሐንዲስ አጣን፣ እሱ የአትሌቲኮ ማድሪድ ወርቃማ ዘመን የቀየሰ ድንቅ ሰው ነው›› ሲል ገልፆታል። የአትሌቲኮ ማድሪድ የቀድሞ ተጫዋች፣ የአሁን ፕሬዚዳንትና በባርሴሎና ኦሊምፒክ ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ዋንጫ ያነሳው ኪኮ‹‹ አንቲች የፈጠራ ሰው ነው፣ የሊጉንና የኮፓ ዲላሬን ዋንጫ እንድናነሳ አድርጓል፣ እሱ ለእኔ ምርጡ አሰልጣኝ ነው›› በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል። በአንቲች ስር ከሰለጠኑ ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ፖርቹጋላዊው ፓውሎ ፉተር በበኩሉ‹‹አንቲች በአትሌቲኮ ማድሪድ ስለፈፀመው ገድል ለመናገር ቃላት የሉኝም፣ እሱ ለአትሌቲኮ ማድሪድ ብቻ ሳይሆን ለእግር ኳስም ጀግና ነው፣ ነብሱን ይማር›› ብሏል። የቀድሞው የሊቨርፑልና አትሌቲኮ ማድሪድ ኮከብ ፈርናንዶ ቶሬስ በአንቲች አሰልጣኝነት ስር የማይረሳ ትዝታ ካላቸው ተጫዋቾች አንዱ ነው። ‹‹አንቲች ጥሎን ሄዷል፣ እሱ እግር ኳስን ያስከበረ ጀግና ነው፣ በአትሌቲኮ ማድሪድ የድል ታሪክ ውስጥ ሁልጊዜም ሲዘከር ይኖራል›› በማለት ቶሬስ ሐዘኑን ገልጿል። አንቲች በአሰልጣኝነት ዘመኑ ባሰለጠናቸው ተጫዋቾች ብቻም ሳይሆን በተቀናቃኝ ክለብ ተጫዋቾች ክብር የሚሰጠው መሆኑን የሪያል ማድሪዱ ተከላካይና አምበል ሰርጂዮ ራሞስ አስተያየት ምስክር ይሆናል። ራሞስ ‹‹ተቀናቃኛችን አትሌቲኮ ማድሪድን ታላቅ ክለብ አድርጓል›› በማለትም ሐዘኑን ገልጿል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 4/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=30231
[ { "passage": "ወርቃማ በሚባለው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ዘመን የያኔው ሐረርጌ ክፍለ ሃገር ክለቦች የብሔራዊ ቡድኑ ጥንካሬና የጀርባ አጥንት በመሆን ዛሬ ላይ የምንዘክራቸው በርካታ ከዋክብት ተጫዋቾችን አበርክተዋል። በ1952፣ 54፣ 55 እና 57 ዓ.ም ለአራት ዓመት ጥጥ ማህበር (ኮተን)፣ ከ1953 እስከ 1956 ደግሞ ድሬዳዋ ሲሚንቶ ከክልላቸው አልፈው የኢትዮጵያ ቻምፒዮን ሆነዋል። በ1990 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በቂ ጥናት ሳይደረግበት፣ ያለ ጊዜው ከተወለደ በኋላ የከተማ ወይም ክልል ቻምፒዮናዎች ቀስ በቀስ ደብዛቸው እየጠፋ ሄዷል። የከረረው የድሬ ጸሐይ ሳይበግረው በየሳምንቱ የከተማውን ክለቦች ፍልሚያ ይመለከት የነበረው የዚያ ዘመን ትውልድ እግር ኳስ አፍቃሪ ዛሬ በአንድ ክለብ ብቻ ቀርቶ በሁለት ሳምንት አንድ ጊዜ የድሬዳዋ ከተማ ጨዋታን ብቻ መመልከት እጣፋንታው ሆኗል። ይህም አንድ ለእናቱ የሆነው የድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ለበርካታ ዓመታት ፕሪሚየር ሊግ ላይ ተሳታፊ መሆን ተስኖት ምስጋና ለሴቷ አሰልጣኝ መሰረት ማኔ ይሁንና ከሦስት ወይም አራት ዓመታት ወዲህ ነው በፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ለመሆን የበቃው። አሁንም ቢሆን ድሬዳዋ ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ ከዓመት ዓመት ላለመውረድ እንጂ ለዋንጫ ተፎካካሪ ክለብ ሆኖ ደጋፊዎቹን የሚያረካና የሚመጥን ደረጃ ላይ መድረስ አልቻለም። እንደ ድሬዳዋ ሁሉ\nየአዲስ አበባ\nእግር ኳስም\nፕሪምየር ሊግ\nአመጣሽ በሆነ\nነቀርሳ ቀስበቀስ\nወደ ሞት\nእያዘገመ ነው።\nበሊጉ ላይ\nየአዲስ አበባ\nክለቦች ቁጥር\nእያደር እየከሰመ፣\nተጽኗቸውም እየተዳከመ\nሄዷል። የዚያኑ\nያህል በከተማዋ\nየነበሩ ትልልቅ\nክለቦች ከዓመት\nዓመት ከአይን\nእየተሰወሩ ይገኛሉ።\nየመንግስት የልማት\nተቋማት ክለቦች\nቁጥር እየቀነሰ\nየከነማ ክለቦች\nቁጥር እያበበ\nበሄደበት በዚህ\nዘመን የሸገር\nክለቦች አዲስ\nፈተና ለመጋፈጥ\nተገደዋል። ፕሪሚየር\nሊጉ ከተጀመረበት\n1990 ዓ.ም\nወዲህ እንኳን\nበአገራችን እግር\nኳስ ወጣቶችን\nበማፍራት ለብሔራዊ\nቡድኑ በመመገብ\nየሚታወቀው የሁለት\nጊዜ ቻምፒዮኑ\nመብራት ሃይል፣\nንግድ ባንክና\nመድንን የመሳሰሉት\nክለቦች ከሊጉ\nመውረድ ብቻ\nሳይሆን መፍረስም\nእጣ ፋንታቸው\nሲሆን ተመልክተናል።የከነማ ክለቦች ቁጥር መብዛት በመርህ ደረጃ መልካም መሆኑን በርካታ የስፖርት ቤተሰቦች የሚስማሙበት ቢሆንም የክለቦቹ የፋይናንስ አጠቃቀም በጤናማ መንገድ እስካልተጓዘ ድረስ የሚያስከትለው ውጤት የከፋ እንደሚሆን መገንዘብ ይቻላል። የከተማ ክለቦች የግብር ከፋዩን ህዝብ ገንዘብ በተጋነነ መጠን እግር ኳሱ ላይ ማፍሰሳቸው መሟላት ያለባቸው ብዙ ማህበራዊ አገልግሎቶችና ተንዶ የማያልቅ ችግሮች ላሉባቸው ከተሞች በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ነው። የፋይናንስ ጨዋነት ደንብ ባለመኖሩም የተጫዋቾች ደመወዝና የፊርማ ክፍያ ግሽበት ከስፖርትም የዘለለ ዓላማ ያነገቡትን አንዳንድ\nየክልል ክለቦች\nቅጥ ላጣ\nወጪና ብክነት\nአጋልጧቸዋል። ይህም\nበቀጥተኛነት በታክስ\nከፍዩ ህዝብ\nገንዘብ ላይ\nያልተንጠላጠሉትን ህዝባዊ\nየሆኑ እግር\nኳስ ክለቦችን\nለፈተና ዳርጓል።\nበተለይም ቅዱስ\nጊዮርጊስና ኢትዮጵያ\nቡና እንደ\nከነማ ክለቦች\nእጅግ ከፍተኛ\nዓመታዊ በጀት\nየመመደብ አቅምና\nእምነትም የላቸውም\nወይም አቅሙን\nእያጡ መጥተዋል።\nተጫዋቾች በሌሎች\nክለቦች ከፍ\nያለ ክፍያ\nየሚከፈላቸው መሆኑ\nእያደገ ከቀጠለ\nሁለቱን የሸገር\nክለቦች የመምረጥ\nዕድላቸው ጠባብ\nእየሆነ መሄዱ\nየግድ ነው።\nበዚሁ የክለቦቹ\nተፎካካሪነትም አብሮ\nመዳከሙን እንደሚቀጥል\nከወዲሁ አርቆ\nመመልከቱ አይከፋም።እንደ ኢትዮጵያ\nእግር ኳስ\nፌዴሬሽን የሪፎርም\nጥናት ከሆነ\nበፕሪምየር ሊጉ፣\nበከፍተኛ ሊግና\nበአንደኛ ሊግ\nእስከ ግንቦት\n30 ድረስ የመንግስት\nክለቦች የጨረሱት\nበጀት 2 ነጥብ\n2 ቢሊዮን ብር\nይደርሳል። እስከ\nሰኔ 30 ድረስ\nያለውን ጨምረን\nካሰላን ዘግናኝ\nውጤት እንደምናገኝ\nከግምት ይግባ።\nበፕሪምየር ሊጉ\nላይ የሚሳተፉ\nየከተማ ክለቦች\nዝቅተኛ ዓመታዊ\nበጀት የሚባለው\n58 ሚሊዮን ብር\nመሆኑን አንድ\nአንድ መረጃዎች\nይጠቁማሉ። የክልል\nከተማ ክለቦች\nአቅም እየፈረጠመ\nእግር ኳሱ\nላይ የሚያፈሱት\nመዋዕለ ንዋይ\nእየገዘፈ በሄደ\nቁጥር እንደ\nኢትዮጵያ ቡናና\nቅዱስ ጊዮርጊስ\nአይነት ህዝባዊ\nክለቦች ከዚህ\nበኋላ የዋንጫ\nተፎካካሪ የሚሆኑበት\nዘመን ቅርብ\nእንደማይሆን ብዙዎች\nምክኒያታዊ ስጋት\nአላቸው።ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተወዳዳሪ ክለቦች ብዛት ሲጀምርም ጥናት ያልተደረገበት መሆኑ እያደር በእያንዳንዱ ክለብና በአገራችን እግር ኳስ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን በማስረጃ መመልከት ይቻላል። የፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ክለቦች ብዛት ከ12 ወደ 14፣ ከ14 ወደ 16 ያደገበት አሳማኝ ምክንያት የለውም። የሊጉ ክለቦች ቁጥር 14 በነበረበት በ2004 ዓ.ም መቀመጫቸውን ሸገር ላይ ያደረጉ ክለቦች ብዛት ሰባት ነበር። በእርግጥ በዚያ ዘመን የሸገር ክለቦች የሊጉን እኩሌታ ቁጥር መያዛቸው በሌሎች የክልል ክለቦች ላይ የማይገባ የፉክክር ጥቅም ያስገኝላቸው እንደነበር መካድ አይቻልም። በሰንጠረዡ ግርጌ የጨረሰው ፊንጫ ስኳር በመኪና እየተዟዟረ ተዳክሞ ሲጫወት፣ ሰባቱ ክለቦች ብዙሃኑን የሊግ ጨዋታዎች ያለጉዞ ድካም በአዲስ አበባ ያካሂዱ ነበር። በዚያ ዓመት በሰንጠረዡ እስከ አራተኛ የነበረውን ቦታ ይዘው ያጠናቀቁት የአዲስ አበባ ክለቦች መሆናቸው አያስገርምም። የእግር ኳስ ተንታኙ ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ በማህበራዊ ድረ-ገፅ ይፋ ያደረገው ስታስቲክስ እንደሚጠቁመው በሊጉ በጨዋታ የሚቆጠረው አማካይ የጎል መጠን 2 ነጥብ 34 የነበረ ሲሆን እስካለንበትም 2011 ድረስ ይህን ያህል ጎል በአማካይ የተመዘገበበት ዓመት ከዚያ ወዲህ አልታየም። የዘንድሮው ደደቢት በደረሰበት ከባድ የፋይናንስ ችግር ምክንያት ስብስቡን በማሳሳቱ ዘንድሮ የሊጉ እጅግ ደካማው ቡድን በመሆን በዘጠኝ ዓመታት ከታየው ሁሉ መጥፎውን የጎል ዕዳ ይዞ ወርዷል። ይህም የሊጉን የጎል ብዛት ያለምክንያት አሳድጎታል። የ14\nክለቦች ሊግ\nከ16 ክለቦች\nሊግ የተሻለ\nመሆኑን ማየት\nተገቢ ነው።\n14 ክለቦች የሚፎካከሩበት\nሊግ በጨዋታዎች\nመካከል በቂ\nየማገገሚያ ጊዜ\nየሚሰጥ መርሐግብር\nስለነበር በንጽጽር\nያልተዳከሙ ተጫዋቾች\nበየጨዋታው የመገኘታቸው\nዕድል ከፍ\nያለ ሲሆን\nየጨዋታውም ግለት\nየተሻለ እንደሚሆን\nጥርጥር አይኖርም።\nበኢትዮጵያ የሊግ\nክለቦች ቁጥር\nየሚጨመርበትና የሚቀነስበት\nበጥናት የጎለበተ\nስፖርታዊ ምክንያት\nየለም። ሌላው\nቢቀር በዓመት\nየ58 ጨዋታ\nልዩነት ስለፈጠረ፣\nየኢትዮጵያ ጥሎ\nማለፍ ዋንጫ\nከሊጉ መርሃግብር\nጋር ተጣጥሞ\nየመከናወኛ ጊዜ\nበማጣቱ ለዛ\nቢስ እንዲሆን\nምክንያት መሆኑን\nማየት ይቻላል።የሊጉ ተወዳዳሪዎች\nብዛት በመደበኛነት\n16 ሲደረግ የሊጉ\nአማካይ የጎል\nመጠን እያሽቆለቆለ\nመጥቷል። በሊጉ\nየአዲስ አበባ\nክለቦች ብዛት\nበቀነሰ ቁጥር\nየቅዱስ ጊዮርጊስና\nኢትዮጵያ ቡና\nጎል የማስቆጠር\nአቅም እየወረደ\nሊሄድም ተገዷል።\nበስምንት ዓመት\nውስጥ የቅዱስ\nጊዮርጊስ የዓመቱ\nመጨረሻ የግብ\nክፍያ ከ39\nወደ 10 አሽቆልቁሏል።\nየሊጉ የጨዋታ\nአማካይ ጎል\nመጠንም ከ2004\nእስከ 2010 ባለው\nየጊዜ ርቀት\nበጨዋታ በአማካይ\nበ0 ነጥብ\n48 ጎል ቀንሷል።\nያለግብ የሚጠናቀቁ\nጨዋታዎች ብዛት\nእየጨመረ፣ የሊጉ\nአዝናኝነት እየቀነሰ\nሲመጣም ተስተውሏል።በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ቡና ጉዳይ ይበልጥ አስደንጋጭ ይመስላል። የሊጉ ቻምፒዮን ከሆነበት ከ2003 ወዲህ በየጨዋታው የሚሰበስበው አማካይ ነጥብ\nከ 2 ነጥብ\n1 ወደ 1 ነጥብ\n3 አሽቆልቁሏል። በሊጉ\nላይ ሰባት\nየአዲስ አበባ\nክለቦች በነበሩበት\n2003 እና ሶስት\nብቻ በቀሩበት\nበ2011 መካከል\nቡና በአማካይ\nበየጨዋታው የ\n0ነጥብ 8 ነጥብ\nማሽቆልቆል አሳይቷል።\nበተመሳሳይ በጎል\nመጠንም ቢሆን\nበሁለቱ ዘመናት\nመካከል በጨዋታ\n0 ነጥብ 8 ግብ\nቀንሷል። ሊጉ\nበዚሁ መልኩ\nከቀጠለ፣ ሁለት\nየሸገር ክለቦች\nብቻ በቀሩበት\nበ2012 የኢትዮጵያ\nቡና ዕጣ\nምን ይሆናል?\nየሚለውን ስንመለከት\nእውነትም አስደንጋጭ\nመሆኑን መረዳት\nይቻላል።የቅዱስ ጊዮርጊስም\nነገር እንዲሁ\nሳይታይ መታለፍ\nየለበትም። ከፍተኛ\nጎል ካስቆጠረበት\nከ2006 ወዲህ\nበአምስቱ ዓመታት\n‹‹የጎል ምርቱ››\nቀንሶበታል። ቢያንስ\nየ27 ጎሎች\nልዩነት አሳይቷል።\nይህ የሆነው\nበዘንድሮው ውድድር\n‹‹ፈረሰኞቹ ሶስት\nጨዋታዎችን ባለመጫወታቸው\nነው›› የሚል\nሙግት ሊነሳ\nይችላል። ነገር\nግን ሶስቱን\nጨዋታዎች ቢጫወቱና\nበእያንዳንዳቸው ስምንት፣\nስምንት ጎሎችን\nቢያስቆጥሩ እንኳን\nልዩነቱ የሚጠብ\nአይሆንም። በ2006\nአንድ ክለብ\n26 ጨዋታዎች ሲጫወት፣\n30 ጨዋታዎች ከሚያደርግበት\n2011 ጋር በአራት\nጨዋታ እንደሚያንስም\nልብ ማለት\nይገባል። የጨዋታዎች\nቁጥር በዝቶ\nየጎሉ መጠን\nይህን ያህል\nዝቅ የሚልበት\nአንድ አንገብጋቢ\nምክንያት ከሌለ\nበስተቀር በጤና\nእንዳልሆነ ግልጽ\nነው።ስፖርታዊ ባልሆኑ\nምክንያቶች በተለይ\nከሜዳ ውጭ\nተጉዞ ማሸነፍ\nብርቅ በሆነበት\nበዚህ ዘመን\n2012 ላይ የሊጉን\nባህሪ በአዎንታ\nየሚቀይር ሰማያዊ\nተዓምር ሊመጣ\nአይችልም። አካሄዱ\nሁሉ ነገር\nከድጡ ወደ\nማጡ እንደሚሆን\nምልክቶች መታየት\nከጀመሩ ሰነባብተዋል።\nጨዋነት የሚታይባቸው\nየክልል ክለቦች\nያሉ ቢሆንም፣\nበተጫዋቾች ላይ\nየስጋት ሸክም\nየሚጭኑ ስታዲየሞች\nየተበራከቱበት ሊግ\nላይ ተጫዋችም\nሆነ አርቢትር\nበሜዳ ላይ\nያለጭንቀት፣ በስፖርታዊ\nመንፈስ ውስጥ\nብቻ መቆየት\nአይችሉም። ክለቦቹ\nበራሳቸው ሜዳ\nእንደዕለቱ ብቃታቸው\nየላባቸውን የሚያገኙ\nከሆነና በክልል\nግጥሚያዎች ሆን\nብለው ለመሸነፍ\nየሚገደዱ ከሆነ\nከዚህ በኋላ\nየትኞቹም ክለቦች\nበልፋታቸው ልክ\nየዘሩትን ያጭዳሉ\nለማለት ይቸግራል።ይህም የከተማዋን\nክለቦች የፉክክር\nዕድል አደጋ\nላይ ይጥለዋል።\nበ2012 ከምንጊዜውም\nበበለጠ የሸገር\nክለቦች በጉዞ\nይደክማሉ፣ ከሜዳ\nውጪ ጨዋታዎቻቸው\nይበዛል። ከ2011\nይልቅ ወደ\nሶስት አዳዲስ\nየክልል ሜዳዎች\nተጉዘው የመጫወት\nግዴታ አለባቸው።\nበመከላከያ እግር\nኳስ ክለብ\nስንብት ምክንያት\nአዲስ አበባ\nበዓመት 30 ብቻ\nየሊግ ጨዋታዎች\nየሚደረጉባት ከተማ\nሆናለች። የከተማዋ\nክለቦች ከከተማዋ\nበራቁ ቁጥር\nደግሞ የሁለቱ\nአንጋፋ ክለቦች\nአሸናፊነት ዕድል\n(ስፖርታዊ በሆኑም\nይሁን ባልሆኑ\nምክንያቶች) እየቀነሰ\nመሄዱ አዲስ\nአበባን በእግር\nኳስ ቀጣይዋ\nድሬዳዋ ሊያደርጋት\nእንደሚችል ግልፅ\nይመስላል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 27/2011 ቦጋለ\nአበበ", "passage_id": "8d92ecf5b998ad44d0e102922b933bee" }, { "passage": "በጨዋታው ስታምብራስ 1-0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ ብቸኛውን የድል ጎል ናስሮ ቦውቻሬብ በ84ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል፡፡ ድሉን ተከትሎ ስታምብራስ በ2018/19 የዩሮፓ ሊግ ውድድር ላይ ተሳታፊ መሆኑን ከወዲሁ አረጋግጧል፡፡ ክለቡን በጃንዋሪ 2017 የተረቡትና በ2006 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ያሰለጠኑት አሰልጣኝ ማርያኖ ባሬቶም የመጀመርያ ድላቸውን ከክለቡ ጋር አጣጥመዋል፡፡በክለቡ ስብስብ ውስጥ የሚገኘው ኢትዮጵያዊው ሶፎንያስ መኳንንት አስረስ በቀጣዩ አመት በዩሮፓ ሊግ ላይ ሊጫወት የሚችል ተጫዋች ነው፡፡ የቀኝ መስመር አማካዩ ከስታምብራስ የወጣት ቡድን በ2017 ወደ ዋናው ቡድን ያደገ ሲሆን በተለያዩ የፖርቱጋል ክለቦች የሙከራ ጊዜ አሳልፎ ወደ ክለቡ ተመልሷል፡፡በዘንድሮው የዩሮፓ ሊግ የአልባንያው ኬኤፍ ስከንደብሩ ወደ ምድብ ጨዋታዎች ሲያልፍ ኢትዮጵያዊው አማካይ ቢንያም በላይ የቡድኑ አባል እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡\nበ2009 የተመሰረተው ስታምብራስ በፖርቹጋላዊያን ባለሀብቶች የሚተዳደር ሲሆን አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶም በክለቡ የአክሲዮን ድርሻ እንዳላቸው ታውቋል፡፡", "passage_id": "c20626ac9aca73a3c51b8d15f54728bb" }, { "passage": "ፓሪሴንት-ጀርሜይን ጋር የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫ እና ከሲቪያ ጋር ሶስት የዩሮፓ ሊግ ዋንጫዎችን ማንሳት የቻሉት ኡናይ ኤምሪ በአርሰናል አመርቂ ውጤት ማምጣት ባለመቻላቸው ዛሬ የክለቡ አስተዳደር እንዳሰናበታቸው ገልጿል።\n\n• የስኮትላንድ እግር ኳስ ማህበር ታዳጊዎች ኳስ በቴስታ እንዳይመቱ ሊያግድ ነው \n\n• ከመኪኖች ይልቅ ብስክሌቶች የሚበዙባት ከተማ \n\nክለቡ ቋሚ አሰልጣኝ እስኪያገኝ ድረስ፤ በረዳት አሰልጣኝ እና በቀድሞ የአርሰናል አማካይ ፍሬዲ ሉንበርግ በግዜያዊነት ይሰለጥናል ተብሏል። \n\nመድፈኞቹ ባለፉት 7 ጨዋታዎች ማሸነፍ ሳይችሉ የቀሩ ሲሆን፤ ትናንት ምሽት የዩሮፓ ሊግ የምድብ ጨዋታ በሺዎች በሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው ፊትና በሜዳቸው በጀርመኑ ክለብ ኢንትራ ፍራክፈርት 2 ለ 1 ተሸንፈዋል። \n\nለመሆኑ ተሰናባቹ ኡናይ ኤምሪን ማን ሊተካቸው ይችላል?\n\nኑኖ ኤስፒሪቱ ሳንቶስ\n\n1. ኑኖ ኤስፒሪቶ ሳንቶስ \n\nኡናይን ይተካሉ ተብለው ከተገመቱ አሠልጣኖች መካከል በዋነኛነት ስማቸው እየተነሳ ያለው የወቅቱ የዎልቨርሃምፕተን አሠልጣኝ ኑኖ ኤስፔሪቶ ሳንቶስ ናቸው። \n\nኑኖ ኤስፒሪቶ ሳንቶስ ዎልቭስን ይዘው በፕሪሚየር ሊጉ ሰንተረዥ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠው ይገኛሉ። \n\nማክሲሚሎኢያኖ አሌግሪኒ\n\n2. ማሲሚላኖ አሌግሪ \n\nስካይ ስፖርት እንደዘገበው ኡናይ ኤምሪ ከአርሰናል ከተለያዩ በኋላ በማሲሚላኖ አሌግሪ እና በአርሰናል ክለብ መካከል ግንኙነቶች ተጀምሯል። \n\nበቅርቡ ከጁቬንቱስ የተለያዩት አሌግሪ ከአሮጊቷ ጋር ውጤታማ የሚባል ጊዜን አሳልፈዋል። \n\nአሌግሪ ከጁቬንቱስ ጋር አምስት የሴሪያአ እና አራት ኮፓ ኢታሊያ ዋንጫዎችን ከማንሳታቸውም በተጨማሪ ሁለት ጊዜ ለቻምፒያንስ ሊግ ፍጻሜ መድረስ ችለዋል። \n\nካርሎ አንቾሎቲ\n\n3. ካርሎ አንቾሎቲ \n\nናፖሊን እያሰለጠኑ የሚገኙት ካርሎ አንቾሎቲ ሌላው ኡናይ ኤምረን ይተካሉ ተብለው ከተገመቱት አሰልጣኞች መካከል ይገኙበታል።\n\n• «የኔ ትውልድ ታሪክ እንደሚሠራ እምነት አለኝ» ሎዛ አበራ \n\nጣሊያናዊው አንቾሎቲ የውድድሩ ዘመን እስኪናቀቅ ድረስ ከናፖሊ ጋር ኮንትራት ቢኖርባቸውም፤ አሰልጣኙ ወደ ኤምሬትስ ሊያቀኑ እንደሚችል በስፋት እየተዘገበ ነው። \n\nብሬንዳን ሮጀርስ\n\n4. ብሬንዳን ሮጀርስ\n\nሌስተር ሲቲዎች ዘንድሮ ደንቅ የሚባል የውድድር ዘመን እያሳለፉ ይገኛሉ። በብሬንዳን ሮጀርስ የሚመሩት ቀበሮዎቹ ካለፉት 10 ጨዋታዎች አርሰናልን ጨምሮ በድንቅ ጨዋታ 9 ግጥሚያዎችን በድል ማጠናቀቅ ችለዋል። \n\nብሬንዳን ሮጀርስ ወደ ኢሚሬትስ እንዲያቀኑ የበርካታ የአርሰናል ደጋፊዎች ምኞት ነው። \n\nማይክል አርቴታ\n\n5. ማይክል አርቴታ\n\nኡናይ ኤምሪ አርሰናልን እንዲያሰለጥኑ ከመሾማቸው በፊት፤ ክለቡን ለማሰልጠን ስሙ በስፋት ሲነሳ የነበረው ማይክል አርቴታ ነበር። \n\nየቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች ባለፉት ሶስት ዓመታት ከከማንችሰተር ሲቲው ፔፕ ጋርዲዎላ ሥር ሆኖ የአሰልጠኝነትን ክህሎት ሲማር ቆይቷል።\n\nረዳት አሰልጣኙ አርቴታ፤ ማንችሰተር ሲቲ ሁለት የፕሪሚር ሊግ ዋንጫ፣ ሁለት የሊግ ዋንጫዎችን እና ኤፍ ኤ ዋንጫዎች እንዲያነሳ የበኩሉን አስተዋጽኦ አበርክቷል። \n\nፓትሪክ ቪዬራ\n\n6. ፓትሪክ ቪዬራ\n\nሌላው የቀድሞ የአርሰናል ባለታሪክ አማካይ ፓትሪክ ቪዬራ ቀጣዩ የአርሰናል አሰልጣኝ ሊሆን እንደሚችል እየተጠቀሰ ነው።\n\n• የሆንግ ኮንግን የዘር መድልዎ የሚፋለሙ አፍሪካዊያን እግር ኳስ ተጫዋቾች\n\nቪዬራ የማይረሳውን የአርሰናል ወርቃማ የ2003/4 የድል የውድድር ዘመን አንበል በመሆን ክለቡን መርቷል። \n\nየፈረንሳዩን ኒስ እግር ኳስ ክለብ እያሰለጠነ የሚገኘው ቪዬራ የሚፈለገውን ውጤት እያስመዘገበ ባይሆንም፤ መድፈኞቹ የቼልሲን አርዓያ የሚከተሉ ከሆነ፤ ቪዬራ የአርሰናል አሰልጣኝ... ", "passage_id": "382cbb1fccc12b35e0b120face8d1068" }, { "passage": "ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከአንድ ሚሊየን በላይ የዓለምን ሕዝብ ያጠቃው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ያልገባበት ቤት፣ ያላንኳኳው በር የለም። ከዓለም ታላላቅ አገራት መሪዎች እስከ ተራው ሕዝብ፣ ከዝነኛ ሰዎች እስከ ሕፃናትና አዛውንት ድረስ የዚህ አስከፊ ወረርሽኝ ተጠቂ ሆነዋል። ቫይረሱን ለመቋቋም በሽታን የመመከት ከፍተኛ አቅም ያላቸው የስፖርቱ ዓለም ሰዎች ሳይቀሩ በዚህ ወረርሽኝ ተለክፈዋል፣ ሕይወታቸውን ያጡም ጥቂት አይደሉም። የስፖርት ቤተሰቡ በቫይረሱ ስርጭት ስጋት የዓለም ታላላቅ የስፖርት መድረኮች ተቆልፈውበት ሁነኛ የመዝናኛ አማራጩን አጥቶ በየቤቱ ቆዝሟል። የስፖርቱ ዓለም ታላላቅ ከዋክብትም ረብጣ ገንዘብና ዝናቸው ከደጃፋቸው እንዲወጡ አቅም አልሆናቸውም። \nየኮሮና ቫይረስ በስፖርቱ ዓለምና በስፖርት ቤተሰቡ የሚያሳድረው አሉታዊ ተፅዕኖ በሳምንቱ አጋማሽ ወደ ሃዘን የቀየረ አጋጣሚ ፈጥሯል። ፈረንሳዊው እውቅ የስፖርት ጋዜጠኛ ፔፕ ዲዉፍ ባለፈው ረቡዕ በኮሮና ቫይረስ ምክኒያት ሴኔጋል መዲና ዳካር ውስጥ በስልሳ ስምንት ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የመለየቱ ዜና ተሰምቷል። ይህም በመላው ሴኔጋልና አፍሪካ እንዲሁም ፈረንሳይ ትልቅ የስፖርቱ ዓለም አሳዛኝ ክስተት ሆኗል። \nትውልዱን በቻድ አቢቼ ያደረገው ዲዉፍ ከሴኔጋላዊ ቤተሰቦች የተገኘ ሲሆን የቻድ፣ ሴኔጋልና ፈረንሳይ ዜግነት አለው። ገና የአስራ ሰባት ዓመት ወጣት እያለ ለብቻው ወደ ፈረንሳይ ያቀናው\n ዲዉፍ የፖለቲካል ሳይንስ ካጠና በኋላ የፈረንሳዩ ክለብ ኦሊምፒክ ደ ማርሴል ጋዜጣ ላይ ፅሁፎችን በማበርከት ነበር ወደ ስፖርት ጋዜጠኝነት ሕይወት የገባው። ይህም በኋላ ላይ የተጫዋቾች ወኪል ሆኖ ለመስራቱ ትልቅ በር የከፈተለት አጋጣሚ እንደነበር የታሪኩ ፀሐፊዎች ይናገራሉ። ዲዉፍ የተጫዋቾች ወኪልነት ስራውን የጀመረው የቀድሞውን ፈረንሳዊ ተከላካይ ባሲል ቦሊ እንዲሁም ካሜሩናዊው ግብጠባቂ ጆሴፍ አንቶኒ ቤልን ወደ ማርሴል ክለብ በማምጣት ሲሆን በሂደት ዊሊያም ጋላስ፣ ሳሚር ናስሪና ሌሎችም እውቅ ተጫዋቾችን በደንበኝነት ይዞ ወኪል በመሆን አገልግሏል። በተለይም ኮትዲቯራዊው ኮከብ ዲዲየር ድሮግባ እኤአ ከ2003 እስከ 2004 በማርሴል ቆይታው ወቅት ወኪሉ በመሆን የተሳካ ጊዜ እንደነበረው ይጠቀሳል። \nይህም በእርግር ኳስ ውስጥ የነበረው የነቃ ተሳትፎ እኤአ 2005 ላይ የማርሴል ክለብ ፕሬዚዳንት እስከ መሆን አድርሶታል። ዲዉፍ በአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች የሚሳተፍ ክለብ ፕሬዚዳንት ሲሆን በታሪክ የመጀመሪያው ጥቁር ሆኖ ይነሳል። ዲዉፍ የማርሴል ክለብ ፕሬዚዳንት ሆኖ ሲያገለግል ክለቡ በፈረንሳይ የመጀመሪያው ሊግ ሁለት ጊዜ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ ትልቅ ሚና ነበረው። እኤአ 2009 ላይም ዲዉፍ አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሾን ወደ ማርሴል በማምጣት ክለቡ የሊጉን ዋንጫ እንዲያነሳ አድርጓል። ይህም ክብር ክለቡ ከአስራ ስምንት ዓመታት በኋላ ያጣጣመው ሆኖ ተመዝግቧል። አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሾ ባለፈው የሩሲያ ዓለም ዋንጫ ፈረንሳይ ከሃያ ዓመታት በኋላ ስታሸንፍ የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ እንደነበሩ አይዘነጋም። ከዚህ\n ድል በኋላ ከክለቡ ፕሬዚዳንትነት የለቀቀው ዲዉፍ የፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበርን መርቷል። እኤአ 2009 ላይ በፊፋ ጠቅላላ ጉባዔ ዙሪክ ላይ ተገኝቶ በፈረንሳይ እግር ኳስ ደረጃና በአጠቃላይ እግር ኳስ ውስጥ ስላለው ዘረኝነት ያደረገው ንግግር በታሪኩ ይጠቀስለታል። \nዲዉፍ በአውሮፓ እግር ኳስ ውስጥ አሳሳቢ ስለሆነው የዘረኝነት ጉዳይ ጥቁሮች ሰለባ እንዳይሆኑ በጠንካራ ቃላት በዓለም ሕዝብ ፊት ቆሞ በመሟገት ይታወቃል። በስፖርት ጋዜጠኝነት ሕይወቱም ብዙዎችን በማንቃትና ጠንካራ ስራዎችን በማቅረብ የተጨበጨበለት መሆኑን በርካቶች ይመሰክሩለታል። \nበዚህ ወቅት ዓለምን እያስጨነቀ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ተይዞ የነበረው ዲዉፍ በቤተሰቦቹ አገር ሴኔጋል እርዳታ እየተደረገለት የቆየ ሲሆን ለተሻለ ሕክምና ወደ ፈረንሳይ ለማቅናት በተዘጋጀበት ወቅት ሕይወቱ ማለፉ ተዘግቧል። ይህም በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ በሴኔጋል የተመዘገበ የመጀመሪያው የሞት ዜና ሆኗል። ይህንንም ተከትሎ በርካታ የእግር ኳሱ ዓለም ከዋክብቶች በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን ሃዘናቸውን እየገለፁ ይገኛሉ። \nዲዉፍ ድንቅ ታሪክ የሰራለት ማርሴል ክለብ በትዊተር ገፁ ‹‹ፔፕ ሁል ጊዜም በማርሴል ልብ ውስጥ ይኖራል፣ የማርሴል የምን ጊዜም ታሪካዊ ሰው ነው›› በማለት ሃዘኑን ገልጿል። የፕሮፌሽል ተጫዋቾች ማህበር በበኩሉ ‹‹ጋዜጠኛ፣ወኪልና የቀድሞ የማርሴል ፕሬዚዳንት ፔፕ ዲዉፍ ሕይወቱን ሙሉ እግር ኳስን ሲያገለግል የኖረ ሰው ነው›› በማለት አስታውሶ ሃዘኑን ገልጿል። ፈረንሳዊው የቀድሞ የሊቨርፑል አጥቂ ጅብሪል ሲሴ ዲዉፍ የማርሴል ፕሬዚዳንት እያለ ለክለቡ ተጫውቷል።‹‹የፈረንሳይ እግር ኳስ ዛሬ ድንቅ ሰው አጥቷል›› በማለት ሲሴ የተሰማውን ሃዘን በትዊተር ገፁ አስፍሯል። ሌላኛው ፈረንሳዊ የማንቸስተር ሲቲ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ቤንጃሚን ሜንዲ በበኩሉ ‹‹ድንቅ የክለብ ፕሬዚዳንት ነው፣ ከዚያም በላይ ሁል ጊዜ ለማርሴል እሴቶች የሚጨነቅ ትልቅ ሰው ነው›› በማለት ተናግሯል።\nአዲስ ዘመን መጋቢት 27/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "1b08f73865713f1e30bc30dc44f23f87" }, { "passage": "ሮናልዲንሆን ከሌሎች ብራዚላውያን ተጫዋቾች ልቆ ልዩ የሚያደርገው ነገር አለ። ይሄም በብሄራዊ ቡድን ውስጥ በሁሉም የእድሜ ክለል ላይ የሚደረጉ ለዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ መሳተፉ ነበር። በ1997 የፊፋ በግብፅ ባካሄደው ከ17 አመት በታች የዓለም ዋንጫ፣ በ1999 የደቡብ አሜሪካ ወጣቶች የእግር ኳስ ሻምፒዮና ከ20 ዓመት በታች እንዲሁም በዚያው ዓመት በተመሳሳይ ናይጄሪያ ውስጥ በተሰናዳው የዓለም ወጣቶች ዋንጫ ውድድሮች ላይ ተካፋይ ሆኗል። በዚህም የሚከተሉትን ስኬቶች አግኝቷል። ሮናልዲንሆ በብራዚል ብሄራዊ ቡድን በተለያዩ የእድሜ ደረጃዎች የጫወተ ሲሆን በ1999 ኮፓ አሜሪካን ውድድር ላይ ላቲቪያን 3ለ0 በሆነ ውጤት ብራዚል ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ዋንጫ ማንሳት ችሏል። በዚያው አመት በተመሳሳይ ወር ላይ በተካሄደው የፊፋ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ በተደረጉት እያንዳንዱ ጨዋታዎች ላይ ከዋንጫ ጨዋታው በስተቀር ለብሄራዊ ቡድኑ ግብ ማስቆጠር ችሏል። በዋንጫ ጨዋታው ላይ ብራዚል በሜክሲኮ የ4ለ3 ሽንፈት ደርሶባት ዋንጫውን ማግኘት ባትችልም ኮንፌዴሬሽን ካፕ ጎቾ የ«ጎልደን ግሎብ» የምርጥ ተጫዋችነት ሽልማት እና የወርቅ ጫማን በግሉ አሳክቷል። በ2000 ላይ ደግሞ ሲድኒ ላይ በተካሄደው ኦሎምፒክ ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር በመጓዝ ተጫውቷል። በቅድመ ኦሎምፒክ ውድድሮች ላይም በሰባት ጨዋታዎች 9 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል። ጎቾ በዓለም ዋንጫ ታሪኩ ከብራዚል ጋር የማይረሳ ትዝታን ያስተናገደው በኮሪያና ጃፓን አስተናጋጅነት በ2002 ዓ.ም ነው። በዚህ ውድድር ላይ በስሙ ሁለት ግቦች እና በርካታ ለግብ የሚሆኑ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ችሏል። በተለይ በግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ላይ ከእንግሊዝ ጋር የተገናኘችውን ብራዚል ጨዋታውን በድል እንድትወጣ ያስቻላትን አስደናቂ ቅጣት ምት አስቆጥሯል። በተለይ ጎሏን ልዩ የሚያደርጋት ከ40 ሜትር ርቀት ላይ የተቆጠረች እና ዴቨድ ሴማንን በእጅጉ የፈተነች በመሆኗ ነበር። በ2005 ሮናልዲንሆ የብራዚል ብሄራዊ ቡድንን በአንበልነት እየመራ የፊፋ ኮንፌደሬሽን ካፕን አንስቷል። በተለይ በውድድሩ በሜክሲኳዊው ኩቲሞክ ብላንኮ የተያዘውን የ9 ጎል ክብረ ወሰን መጋራት ችሏል። በ1999 አሜሪካን ካፕ እንዲሁም በ1997 በፊፋ 17 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮን ዋንጫን አንስቷል። በዋናው የብራዚል ብሄራዊ ቡድን በ97 ጨዋታዎች ተሰልፎ ያስመዘገባቸው 33 ጎሎች ናቸው። ከ1996 ጀምሮ በብራዚል ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በ6 ጨዋታዎች 2 ግብ አስቆጥሯል። ከ1999 ጀምሮ በብራዚል 20 ብሄራዊ ቡድን በ5 ጨዋታዎች 3 ጎሎችን፤ ከ1999 እስከ 2008 በብራዚል 23 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በ27 ጨዋታዎች 18 ጎሎች፤ ከ1999 እስከ 2013 በብራዚል ብሄራዊ ቡድን በ97 ጨዋታዎች 33 ጎሎች አስመዝግቧል። 2006 ለጎቾ ጥሩ ጊዜ አልነበረም። ምክንያቱ ደግሞ አንድ ነው። የዓለም ዋንጫ። እርሱን፣ አድሪያኖን እና ካካን የያዘው ብሄራዊ ቡድን ዋንጫውን ያነሳል የሚል ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶት ነበር። ነገር ግን በግልባጩ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ። ስምንት ውስጥ ቢደርሱም በፈረንሳይ የ1ለ0 ሽንፈት ስለገጠማቸው ከውድድሩ ውጪ ለመሆን ተገደዱ። ጎቾ በዚህ ውድድር ላይ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ አቋሙ ወርዶ ነበር። ዓለምን ያስደነቀው ምርጥ ተጫዋች በዚያን ዓመት ለአገሩ ሊደርስላት አልቻለም። በዚህ የተናደዱት ደጋፊዎችም 7 ነጥብ 5 ሜትር የሚደርሰውን ለክብሩ የተተከለለት ሀውልት ጥቃት አድርሰውበት ነበር።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 6/2011", "passage_id": "ffcf974a46604a52afff06cd614b8c2e" } ]
0fab72ded5333f3998b22a889ec0db02
68e0d292174be376b38240e51c8ccdb4
የዲያጎ ጋርዚያቶ ማረፊያ ታውቋል
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ላይ ትልቅ አሻራን ማሳረፍ የቻሉ አሰልጣኝ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል። ኢትዮጵያ በታሪኳ በዓለም ዋንጫ ከ 20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በማሳተፍ አይረሴ ታሪክ ሰርተዋል። በትውልድ ፈረንሳዊው፤ በዜግነት ጣሊያናዊ ዲያጐ ጋርዚያቶ። በኢትዮጵያን ዘንድ የተለየ አክብሮት የሚሰጣቸው አሰልጣኝ ዲያጎ ጋርዚያቶ ርቀው ከነበሩት የአሰልጣኝነት ሙያ መመለሳቸው ተሰምቷል። የ70 ዓመቱ አዛውንት የዲሞክራቲክ ኮንጎው ክለብ ሴንት ኢሎይ ሉፖፖን ለማሰልጠን ከስምምነት መድረሳቸውን ታውቋል:: እኤአ በ1950 ሌስቲዛ የተወለዱት እኝህ አሰልጣኝ በተጨዋችነት ዘመናቸው የተከላካይ መስመር ተሰላፊ ነበሩ።ከ1984 እ.ኤ.አ ጀምሮ በአሰልጣኝነት ማገልገል ሲጀምሩ የፈረንሳይ ዝቅተኛ ሊግ ክለቦችን በማሰልጠን ነበር የቆዩት። የዲያጎ ጋርዚያቶ የአሰልጣኝነት ምዕራፍ ከፍ እያለ መምጣት የቻለ ሲሆን፤ ጅማሮውም ከኢትዮጵያ ይነሳል። አሰልጣኙ ትልቁን ኃላፊነት የተረከቡት በ2001 እ.ኤ.አ ላይ የኢትዮጵያ ሀ 20 ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ሲመደቡ ነበር። በዚሁ ጊዜም የኢትዮጵያን ወጣት ቡድን በአርጀንቲና ለተደረገው 14ኛው የዓለም ወጣቶች ዋንጫ እንዲሳተፍ አብቅተዋል። የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት ቡድን ዋና አሰልጣኝነት ከለቀቁ በኋላ በተለያዩ የአፍሪካ አገራት በክለብ ደረጃ ሲሰሩ ቆይተው በ2007 እ.ኤ.አ ላይ የቶጐ ብሔራዊ ቡድን ተረክበው ነበር። አሰልጣኝ ዲያጎ ጋርዚያቶ የቶጎ ቆይታቸው ከ2 ወራት አልዘለለም።በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ትልቅ ውጤት በማስመዝገብ የተደነቁ ሲሆን ለሁለት ጊዜያት ያሰለጠኑትን የዲ ሪፖብሊክ ኮንጎውን ቲፒ ማዜምቤ በ2009 እ.ኤ.አ የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ እንዲያሸንፍ አድርገዋል።የአሰልጣኙ ውጤታማነት በመረዳት ቲፒ ማዜምቤ ዳግም በአሰልጣኝነት ቀጥሯቸዋል። እኤአ በ2003 እስከ 04 ቲፒ ማዜምቤን ማሰልጠን የቻሉት ዲያጎ ጋርዚያቶ ክለቡ እኤአ በ2010 ዳግም አሰፈረማቸው። አሰልጣኙ አሰልጣኙን ክለቡን እንዲያሰለጥኑ ዳግም በተሰጣቸው እድል ውጤት አልቀናቸውም ነበር። ከቲፒ ማዜምቤ ጋር ለአንድ ዓመት ቆይታ ካደረጉ በኋላ መለያየት ግድ ብሏቸዋል። የዲያጎ ጋርዚያቶ ቀጣዩ አቅጣጫ ወደ ዋይዳድ ካዛብላንካም ሆነ። የዲያጎ ጋርዚያቶ ቆይታ በተመሳሳይ ውጤት አልባ መሆኑን ተከትሎ ክለቡን ጥለው ዳግም ወደ ኢትዮጵያ መጡ። በእኤአ 2012 ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ኢትዮትጵያ የተመለሱት የ70 ዓመቱ አዛውንት ታሪክን መድገም ሳይችሉ ቀርተዋል። አሰልጣኙ ወደ ሀገራችን ሲመጡ በአወዛጋቢ ሁኔታዎች ዋና ብሔራዊ ቡድኑን በኃላፊነት መያዝ ቢችሉም ፤ ከ2 ወራት በኋላ ተሰናብተዋል።በዚሁ ዓመት ወደ አል ሂላላ ኦምዱር ማን ክለብ ያመሩት አሰልጣኙ የጉዟቸው ምዕራፍ ሁሉ ውጤት አልባ ነበር። የዲያጎ ጋርዚያቶ ከክለብ ወደ ክለብ መሽከርከር በሙያው ውጤት እየራቃቸው ከመምጣቱ ጋር ሰፊ ትችቶችን አስተናግደዋል። አሰልጣኙ በአል ሂላላ ኦምዱርማን ክለብ ጋር ቆይታቸው ውጤት አልባ በመሆኑ ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ተሰናበቱ። እኤአ በ2014 አል ሜሪኤሪክ ክለብ ፊርማቸውን ያኖሩት ጋርዚያቶ ፤ከዚህ ክለብ ጋር ጥሩ የሚባል የሶስት ዓመት ቆይታ አድርገዋል። እኤአ በ2017 ከክለቡ ጋር የነበራቸውን ቆይታ በማጠናቀቅ አል ኢተሃድ ተረክበው ነበር ። የ70 ዓመቱ አዛውንት ከሊቢያው ክለብ አል ኢተሃድ ጋር ከአጭር ጊዜ ቆይታ በኋላ ነበር የተለያዩት። የጣልያን ዜጋ የሆኑት ጋርዚያቶ ከሊቢያ ከተሰናበቱ በኋላ ፈላጊ ክለብ ለማግኘት አዳግቷቸው ነበር። የአሰልጣኙ ፈላጊ ማጣት ደግሞ ከውጤት ጋር የሚያያዝ ሲሆን፤ አዛውንቱ ላለፉት ዓመታት ከሙያው እንዲርቁ ያደረጋቸውም ነበር። በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው ዲያጎ ጋርዚያቶን ወደ ስራ መመለሳቸው ተሰምቷል:: አሰልጣኙ የዲሞክራቲክ ኮንጎው ክለብ ሴንት ኢሎይ ሉፖፖን ለማሰልጠን መስማማታቸው ታውቋል:: የዲያጎ ጋርዚያቶ የውጤታማነት ጀንበር እየጠለቀች ቢሆንም፤ ከአዲሱ ክለባቸው ጋር ለማድመቅ እንደሚታትሩ ይጠበቃል። የ70 ዓመቱ አዛውንት ፈታኙ ጉዞ ከሰማያዊ እና ቢጫ ለባሾቹ ጋር የሚነጉድ ይሆናል:: አዲስ ዘመን ሚያዝያ 6/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=30329
[ { "passage": "ጁቬንቲዩስ ከባርሴሎና ጋር በሚያደርገው የሻምፒዮንስ ሊግ ፍልሚያ ከታላቅ ተቀናቃኙ ሊዮኔል ሜሲ ጋር ይገናኛል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በጨዋታው ዋዜማ ላይ ባደረገው ምርመራ ከኮሮና ቫይረስ አለማገገሙን ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡\nየአምስት ጊዜ የባሎን ዶር አሸናፊው ሮናልዶ 18 ጊዜ ተመርምሮ በሁሉም ቫይረሱ ተገኝቶበታል፡፡\nየ 35 ዓመቱ ፖርቱጋላዊ ለመጀመሪያ ጊዜ ኮቪድ -19 የተገኘበት ከሁለት ሳምንት በፊት በአውሮፓ ሀገራት ሊግ ለሀገሩ ሲጫወት ሲሆን የምርመራ ውጤቱን ተከትሎ ወደ ጣሊያን ከተመለሰ በኋላ ራሱን አግልሎ ይገኛል፡፡\nበምድብ ሰባት የተደለደሉት ጁቬንቲዩስ እና ባርሴሎና ጨዋታቸውን ዛሬ ምሽት በቱሪን ያካሒዳሉ፡፡\nበአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ህግ መሰረት ሮናልዶ በጨዋታው ለመሳተፍ ከጨዋታው 24 ሰዓት በፊት ከቫይረሱ ነጻ መሆን ይጠበቅበት ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ሊሆን አለመቻሉ ትናንት ፕሬዝዳንቱን ላሰናበተው እና በጥሩ አቋም ላይ ለማይገኘው ባርሴሎና መልካም የሚባል ዜና ነው፡፡\n", "passage_id": "1de82d6adbdd8731cb20be125a6d0271" }, { "passage": "ሙጌርዋ ዓመቱን በደቡብ አፍሪካ ኦርላንዶ ፖይሬትስ በመጫወት ያሳለፈ ሲሆን በዓመቱ መጨረሻ ከክለቡ ተለቋል፡፡የሙጌርዋ ወኪል ጆኦፍሪ ካይምባ የመሃል አማካዩ ለፈረሰኞቹ የሁለት ዓመት ውል ለመፈረም መስማማቱን ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግሯል፡፡ ዝውውሩ የተጠናቀቀ መሆኑንም ወኪሉ ጨምሮ ገልጿል፡፡የቀድሞ ዩጋንዳ ረቨንዩ ኦቶሪቲ (ዩአርኤ) ተጫዋች ሙጌርዋ በፓይሬትስ በቂ የመሰለፍ ዕድልን የተነፈገው ሲሆን ስሙ በዝውውር መስኮቱ ከካምፓላ ሲቲ ካውንስል እና ከተለያዩ የደቡብ አፍሪካ ክለቦች ጋር ተያይዞ ሲነሳ ነበር፡፡ኳስን ይዞ የመጫወት አቅም ያለው ሙጌርዋ ለዩጋንዳ ብሄራዊ ቡድን መጫወት ችሏል፡፡ የተከላካይ አማካይ እና የጨዋታ አቀጣጣይ መሆን የሚችለው የ22 ዓመቱ ዩጋንዳዊ በፈረሰኞቹ ቤት ከሃገሩ ልጆች ሮበርት ኦዶንካራ፣ ብራያን ኦሞኒ እና አይዛክ ኢሴንዴ ጋር የሚቀላቀል ይሆናል፡፡ቅዱስ ጊዮርጊስ በተለይ ሰርቢያዊውን አሰልጣኝ ሰርዮቪች ‘ሚቾ’ ሚሉቲን ከ10 አመት በፊት ከቀጠረ በኃላ ወደ ክለቡ በስፋት ዩጋንዳዊንን ሲያስፈርም ይስተዋላል፡፡[socialpoll id=”2385802″][socialpoll id=”2385807″]", "passage_id": "11c700e8edfb3e54ad02c4c59a27596c" }, { "passage": "ረቡዕ ኅዳር 16/ 2013 ዓ.ም ህይወቱ ያለፈው የማራዶናን የቀብር ሥነ ሥርዓት ለማስፈፀም ኃላፊነቱን በዋነኝነት የወሰደው ድርጅት ለሥራው የቀጠራቸው ሦስት ግለሰቦች ናቸው ፎቶ ሲነሱ የሚታዩት።\n\nለሕዝብ ይፋ በሆኑት ሁለት ፎቶዎች ላይ ግለሰቦቹ የሬሳ ሳጥኑ ክፍት ሆኖ እየሳቁና፣ እጃቸውንም ከፍ አድርገው የአውራ ጣታቸውን ምልክት ያሳዩበታልም ተብሏል።\n\nፎቶዎቹም ከፍተኛ ውግዘትና ቁጣን ቀስቅሷል።\n\nየማራዶና ተወካይና ጠበቃ ማቲያስ ሞርላ በበኩላቸው አፀያፊ ነገር እንደተከናወነ ጠቅሰው፤ ፎቶውን ያወጡት አካላት በሕግ አግባብ እጠይቃለሁ ብለዋል።\n\n\"ለጓደኛዬ ትዝታ ስል ይህንን የጭካኔ ተግባር የፈፀመውን ሳልፋረዳው አልተኛም\" በማለት ሞርላ በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።\n\nበቦነስ አይረስ ሴፒሎስ ፒኒየር የቀብር አስፈፃሚ ሥራ አስኪያጅ ማቲያስ ፒኮን ለአገሪቱ ሚዲያ እንደተናገሩት በፎቶው ላይ የሚታዩት ሦስት ሰዎች የሬሳ ሳጥኑን ለማንቀሳቀስ ረዳት አድርገው የተቀጠሩ ናቸው ብለዋል። \n\n\"በተፈጠረው ነገር በጣም ነው ያዘንነው\" በማለት ማቲያስ ፒኮን ለኒውስ ቻናል ተናግረዋል።\n\n\"ቤተሰቡ እኛን አምኖ ነበር፤ ከቤተሰቡም ጋር ለረዥም ጊዜ አብረን ሰርተናል\" ብለዋል።\n\nማቲያስ ፒኮን እንዳሉት ኩባንያቸው ከዚህ ቀደምም ለማራዶና ቤተሰቦች የቀብር ሥነ ሥርዓት እንዳዘጋጁም ገልፀዋል።\n\n\"ቤተሰቦቹ በእኛ ሥራ ይተማመናሉ፤ ለዚያም ነው ይህ ተግባር ልባችንን የሰበረው\" በማለት ተናግረዋል።\n\nአክለውም \"የ75 ዓመቱ አባቴ እያለቀሰ ነው፣ እኔም እያለቀስኩ ነው ወንድሜም እንዲሁ። በከፍተኛ ሁኔታ ጎድቶናል\" በማለት ተናግረዋል።\n\nየማራዶና የቀድሞ ባለቤት ክላውዲያ ቪላፋኔን ስለፎቶዎቹ ሲነገራት በጣም ተበሳጭታ እንደነበረም ማቲያስ ገልፀዋል።\n\nየማራዶና ቤተሰቦች ሕጋዊ እርምጃ ይውሰዱ ማቲያስ ባያውቁም፤ ሆኖም እስካሁን ድረስ ከፎቶዎቹ ጋር ተያይዞ ወንጀል ሪፖርት እንዳልተደረገ ቴላም የተባለ የዜና ወኪል የፍትህ አካላትን ምንጭ አድርጎ ዘግቧል።\n\nማራዶና በትናትንናው ዕለት የተቀበረ ሲሆን ህልፈተ ህይወቱንም ተከትሎ የሦስት ቀን ሐዘን በአገሪቱ ታውጇል።\n\nየሬሳ ሳጥኑ በአርጀንቲና ሰንደቅ አላማ እንዲሁም እግር ኳስ ሲጫወት መለያው በነበረው አስር ቁጥር ማልያ ተሸፍኖ በቦነስ አይረስ የፕሬዚዳንቱ ቤተ መንግሥት ሕዝቡ እንዲሰናበተው ተደርጓል።\n\nበሺህዎች የሚቆጠሩ አድናቂዎቹም የእግር ኳስ ጀግናቸውን ለመሰናበት መጥተው ነበር፤ ሆኖም ፖሊስና በሰልፍ ላይ የነበሩ ለቀስተኞች መጋጨታቸውን ተከትሎ የስንብት ፕሮግራሙ በአጭር ተቋጭቷል።\n\nበበርካቶች ዘንድ የክፍለ ዘመኑ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ የሚወደሰው ማራዶና በልብ ህመም ቦነስ አይረስ አቅራቢያ በምትገኘው ትግሬ ከተማ በቤቱ ውስጥ ነው ህይወቱ ያለፈው።\n\n ", "passage_id": "401f1e6c0ca2afb632bbc93912e7c101" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የሌሶቶ ጉዞውን ጀምሯል፡፡ ወደ ማሴሩ የሚጓዙ 18 ተጫዋቾችን ትላንት ያሳወቁት አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ በተጠባባቂነት ይዘውት የነበረው ደስታ ዮሃንስን 19ኛ ተጫዋች አድርገው ወስደውታል፡፡ደስታ ፓስፖርቱ በጊዜ ባለመጠናቀቁ እና የስዩም ጉዳይ ባለመለየቱ በተጠባባቂነት ተይዞ የቆየ ሲሆን የስዩም ጉዞ ባለመሳካቱ ምክንያት አሰልጣኙ የመስመር ተከላካዩን ክፍተት ለመድፈን በማሰብ ለፌዴሬሽኑ ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት አብሮ ሊጓዝ ችሏል ፡፡\nየሀዋሳ ከተማው የመስመር ተከላካይ መልካም የውድድር ጊዜ እያሳለፈ መሆኑኖ ተከትሎ ለመጀመርያ ጊዜ ለብሔራዊ ቡድን ጥሪ ከቀረበላቸው ተጨዋቾች አንዱ ሆኗል፡፡በተያያዘ ዜና ስዩም ተስፋዬ የፓስፖርቱ ጉዳይ እስከ ዛሬ ጠዋት ተጠናቆ ከቡድኑ ጋር አብሮ ይጓዛልጠ ተብሎ ቢጠበቅም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ ነገር ግን በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ ፓስፖርቱ የሚመጣ ከሆነ ዘይቶም ቢሆን ከዋልያዎቹ  ጋር ሊቀላቀል እንደሚችል ስዩም ለሶከር ኢትዮዽያ ተናግሯል\n” ፖስፖርት እንድሰጥ ተጠይቄ የነበረው ሆቴል እንደገባሁ ነበር፡፡ ኬንያ የሚገኘው ካናዳ ኤምባሲ ቪዛ ጠይቄ ስለነበር ከናይሮቢ በጊዜ ፓሰፖርቴን እንዲያስመጡልኝ ጠይቄ ነበር፡፡ ፌዴሬሽኑም ደብዳቤ የላከ ቢሆንም ምላሽ አልተገኘም፡፡ ጥረት እየተደረገ ነው ፤ ከተሳካ በዚህ ሁለት ቀን የማመራ ይሆናል” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ዜናዎች በብሄራዊ ቡድኑ ዙርያ ", "passage_id": "0ce5dc8bdc9042ab3318a449d12eb3cb" }, { "passage": "በዘንድሮ የውድድር ዘመን ተጠናክረው ለመምጣት እየሰሩ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊሶች ዛሬ ማሊያዊ ዜግነት ያለው አቱሳዬ ኒዮንዶን ወደ ስብስቡ መቀላቀሉ ታውቋል።ይህ የ28 ዓመት አጥቂ ከ2007 ጀምሮ ለሃገሩ እና የደቡብ አፍሪካ ክለቦች መጫወት የቻለ ተጨዋች ነው። ለደቡብ አፍሪካዎቹ ብሎምፎንቴን ሴልቲክ፣ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድ እና ፕሪቶሪያ ዩኒቨርሲቲ የተጫወተው አጥቂው ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመምጣቱ ቀደም ብሎ ያለፉትን ስድስት ወራት በደቡብ አፍሪካ ናሽናል ዲቪዥን ክለብ ሻኩማ በመጫወት አሳልፏል።ኒዮንዶ ከፓትሪክ ማታሲ፣ ኤድዊን ፍሪምፖንግ እና ዛቦ ቴጉዉይ በመቀጠል አራተኛው በፈረሰኞቹ ስብስብ ውስጥ የሚገኝ የውጪ ተጨዋች ሆኗል።", "passage_id": "33c22982a0ae91944c5f6733cbae1e20" } ]
3b15eebee18ecf6f6a811199d6c323de
5ee50a82042d7ab643a57d751bba12ed
ያልነጠፈው የስፖርት ቤተሰቡ ድጋፍ
የቅዱስ ጊዮርጊስና የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ስታድየም አካባቢ ለሚገኙ የጎዳና ተዳዳሪዎች ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ድጋፍ አደረጉ። የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ኮሮና ቫይረስን በጋራ ለመከላከል ይቻል ዘንድ ለበርካታ የጎዳና ተዳዳሪዎች ቫይረሱን ሊከላከሉ የሚችሉበትን የማክስ እና የሳሙና ድጋፍ አድርገዋል። የሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች ከትናንት በስቲያ በአዲስ አበባ ስታድየም በነበረው ልዩ ፕሮግራም ላይ እስከ 350 ለሚደርሱ የጎዳና ተዳዳሪዎች ምሳ አብልተዋል። በምሳ ማብላት መርሃ ግብሩ ላይም ኮሮና ቫይረስን እንዴት መከላከል እንደሚቻል የግንዛቤ ማስበጫ ትምህርት ተሰጥቷል። «መርሃ ግብሩ የተዘጋጀበት ዋና ዓላማም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለጎዳና ተዳዳሪዎች እንደሌላው ማህበረሰብ ‹በአሁን ወቅት ማን አለላቸው› በሚል ከእነሱ ጎን ለመቆም ነው » ሲሉ የክለቦቹ ደጋፊ ተወካዮች ገልጸዋል። በተጨማሪም ከሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች የተሰባሰበው የገንዘብ እርዳታም ገቢው ለእነዚህ የጎዳና ተዳዳሪዎች ሆኖ የመጪውን የፋሲካ በዓል በሌላ ልዩ ፕሮግራም እንዲያሳልፉበት እንደሚደረግ ተገልጿል። የስፖርት ማህበረሰቡ ወገናዊነት በቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች እንደተፈጸመው ሁሉ፤ በሌሎች ማህበራትም በኩል ተግባሩ ተጠናክሮ መቀጠሉን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ አሰልጣኞች ይፋዊ ፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በእግር ኳስ ስፖርት የሚገኙ አሰልጣኞች የኮሮና ቫይረስን ለመቆጣጠርና ለማጥፋት እየተደረገ ባለው ርብርብ በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን ጽፏል። በመሆኑም በእግር ኳስ ሙያ ውስጥ የሚገኙ አሰልጣኞች ድጋፎቹን እስከ ሚያዚያ 06 ቀን 2012 ዓ.ም ረፋድ ድረስ ሲደረግ የነበረ ሲሆን ፤በዚህም 118 ሺ 500 ብር በመሰብሰብ ለሚመለከተው የመንግስት አካል ገቢ ሊደረግ መሆኑ መረጃው አመልክቷል። በዓለማችን የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከልና ለመግታት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተደረገ ላለው ርብርብ የስፖርት ማህበረሰቡ እያደረገ ያለውን አበርክቶ አጠናክሮ መቀጠሉን የሚያስረዳ ተግባር ሆኗል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 6/2012
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=30351
[ { "passage": "ክብሮም ብርሀነ እና ክፍሎም ሐጎስ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርጉ ሰይድ ሐሰን እና ካርሎስ ዳምጠው ለሁለተኛ ግዜ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አድርገዋል።የእግር ኳስ ቤተሰቡ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ እና በወረርሺኙ ተጋላጭ ለሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች የንፅህና መጠበቂያ እና ተያያዥ ድጋፎች ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል። አሁን ደግሞ የስሑል ሽረዎቹ ክብሮም ብርሀነ እና ሰይድ ሐሰን፣ የደደቢቱ ክፍሎም ሐጎስ እና ከሳምንታት በፊት ድጋፍ አድርጎ የነበረው ካርሎስ ዳምጠው የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል። ሰይድ ሐሰን በትውልድ ከተማው ሰለክለካ የሚገኙ አስራ ሁለት አባወራዎች ድጋፍ ሲያደርግ ድጋፉም ከከተማው የሚመለከታቸው አካላት በመተባበር እንዳከናወነው ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ በፊትም ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የገንዘብ ድጋፍ ያደረገው ይህ አጥቂ ስሑል ሽረዎች ወደ ከፍተኛ ሊግ እና ፕሪምየር ሊግ ሲያድጉ ወሳኝ ሚና እንደነበረው ይታወቃል። ሌላው ለሁለተኛ ግዜ ድጋፍ ያደረገው ካርሎስ ዳምጠው ነው። ከሳምንታት በፊት ለሜሪ ጆይ ድጋፍ ያደረገው ተጫዋቹ ለበርካታ አቅመ ደካሞች ድጋፍ ሲያደርግ በአንድ አከባቢም ሕብረተሰቡ እጁን የሚታጠብበት ታንከር አስቀምጧል። ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉት ደግሞ የስሑል ሽረው ተከላካይ ክብሮም ብርሀነ እና የደደቢቱ አማካይ ክፍሎም ሐጎስ ናቸው።ከዚህ በፊት በቁጥር በርካታ የሆኑ ተጫዋቾች ለወረርሺኙ መከላከያ ድጋፍ ማድረጋቸው የሚያታወስ ሲሆን በክለብ ደረጃም ድጋፎች መደረግ ጀምረዋል።", "passage_id": "aea78caedaa282b2135d1e4de41fc42e" }, { "passage": " በር ላይ ካናቴራ የለበሱ ወጣቶች ተራርቀው በመቆም እንግዶችን በክብር እጅ ይነሳሉ፡፡ ወደ ግቢው ሲዘልቁ በሞቀ ሰላምታና ፈገግታ ይቀርብልዎታል፡፡ መምጣትዎ ለምን እንደሆነ ስለሚታወቅ ታላቅ ሰብዓዊ ክብር ይቸርዎታል፡፡ መጋቢት 4 ቀን 2012 የኮሮና ቫይረስ ኢትዮጵያ ውስጥ መገኘቱ ይፋ መደረግ ተከትሎ መንግስትና ህዝብ ወረርሽኙ እንዳይዛመት ዘርፈ ብዙ ጥረቶች በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ወረርሽኑ ከመቆጣጠር ጎን ለጎን በሽታው በፈጠረው ስጋት ለኢኮኖሚያዊ ችግር የተጋለጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ለመደገፍ የተለያዩ የበጎ ፈቃድ እንቅስቃሴዎች በመደረግ ላይ ይገኛሉ ፡፡ ከነዚህ የበጎ ፈቃድና እርዳታ ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎች አንዱ ሰብአዊ ጥምረት የሀገር ፍቅር የበጎ ፍቃደኞች ማህበር እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ተጠቃሽ ነው ፡፡ ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው የሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት ውስጥ ማህበሩ በኮሮና ምክንያት ለተለያዩ ችግሮች ለተጋለጡ ወገኖች ሰብዓዊ ድጋፍ ከማህበረሰቡ በማሰባሰብ ላይ ይገኛል፡፡ የማህበሩ አስተባባሪና መስራች የሆነው አርቲስት ያሬድ ሹመቴ ሀገር እና ህዝብ ችግር ላይ በሚወድቁበት ወቅት መተባበር የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን ያስረዳል፡፡ ማህበሩ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን በማስተባበር ከለጋሾች የተለያዩ የምግብ ፣ የዓልባሳትና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ ላይ እንደሚገኝ ይናገራል፡፡ በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች ለችግር እንዳይጋለጡና በወረርሽኙ ምክንያት የሚደርስባቸው ጉዳት ለመቀነስ በገንዘብና በዓይነት የተለያዩ ድጋፎችን እያሰባሰቡ ፤ እስካሁን የተሰበሰበው እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ለማድረስ በዝግጅት ላይ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ እስካሁንም በማህበሩ ስም በተከፈተ የሂሳብ ቁጥር ከ800ሺ በላይ ብር መሰብሰቡን ፤ በዓይነት ደግሞ 220 ማዳበሪያ ሞኮሮኒ፣ 70 ኩንታል የስንዴ ዱቄት፣ 500 ካርቶን ፓስታ፣ 600 የተለያየ ሊትር መጠን ያለው ዘይት፣ 152 ካርቶን ሳሙና እና 350 ፈሳሽ ሳሙና (የተለያዩ የሊትር መጠን ያላቸው) እንዲሁም የተለያዩ ቁሳቁሶችን ከለጋሾች መገኘቱን ያብራራል ፡፡ ማህበረሰቡ ሊከሰቱ ይችላሉ ተብለው የተገመቱ ችግሮችን ለመከላከል እያደረገ ያለውን ትብብርና መደጋገፍ አጠናክሮ ሊቀጥልበት ይገባል ያለው አርቲስት ያሬድ ፣ የገጠመንን አለምቀፍ ወረርሽኝ እንደ ሀገር ሊቋቋም ተባብሮ መቆም የሚያስፈልግበት ወቅት እንደሆነም ያስረዳል፡፡ በማህበሩ ስም የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በመስጠት ላይ እያለ ያገኘነው ወጣት ዮናስ ምትኩ በበኩሉ ፣ ማህበረሰቡ በሚችለው ሁሉ በመደጋገፍ ይህንን ጊዜ ማለፍ የሚጠበቅበት መሆኑን ይገልፃል:: ኮሮናን ለመከላከልና የሚያፈጥረው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ ለመቋቋም ማህበረሰቡና መንግስት እያረጉ ያሉት እንቅስቃሴ የሚያበረታታ ነው ያለው በጎ ፍቃደኛው ወጣት፣ በህብረት ችግሩን ለመፍታት መንቀሳቀስ ዋነኛ መፍትሄ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 28/2012 ተገኝ ብሩ", "passage_id": "5920ec7a65a31984c0f43f87043f723e" }, { "passage": "ለ5ኛ ጊዜ የተዘጋጀው የኢትዮጵያ ቡና የቤተሰብ ሩጫ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ታጅቦ ታስቦ ውሏል።ከ2008 ጀምሮ በየዓመቱ ሲከናወን የነበረው ይህ የቤተሰብ ሩጫ ዘንድሮ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት መልኩን ቀይሮ ዛሬ ተከናውኗል። በተለይ ክለቡ ቀደም ብሎ ለማግኘት ያሰበውን ገቢ እንዳያጣ እንዲሁም ለደጋፊዎች የተሰጠውን 12 ቁጥር የሚወክል ታሪካዊውን ቀን (12-12-12) ላለማለፍ በታቀደ እቅድ ክለቡ 40 ሺ የመሮጫ ማሊያዎችን በመሸጥ መርሃ ግብሩን አዘጋጅቷል። በወረርሽኙ አስጊነት ምክንያት ደጋፊዎች በአካል ሳይሰባሰቡ ነገር ግን በልብ እና ሃሳብ አንድ ሆነው ያከናወኑት ይህ መርሃግብር የተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ተከናውነውበት ታስቦ አልፏል።በተለይ በዚህ ታሪካዊ ቀን መለያውን የገዙ 40 ሺ ደጋፊዎች በየአካባቢያቸው የችግኝ ተከላ፣ የደም ልገሳ እና የአቅመ ደካሞች የመደገፍ ሥራን ሲያከናውኑ ውለዋል። በተለይ በርከት ያሉ ደጋፊዎች በቀበና አካባቢ በሚገኝ ስፍራ ተሰባስበው የችግኝ ተከላ መርሃግብር ሲያከናውኑ ተስተውሏል። በተጨማሪም በርከት ያሉ የክለቡ ደጋፊዎች ስታደየም አካባቢ በሚገኘው የቀይ መስቀል ማኅበር ቅጥር ግቢ በመገኘት የደም ልገሳ አከናውነዋል።የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ከወጪ ቀሪ 4 ሚሊዮን ብር ለማግኘት ባቀደው በዚህ ታሪካዊ ሩጫ ላይ የተሰበሰበው ገቢ ክለቡን በፋይናንስ ለማጠናከር እንደሚውል ተገልጿል።", "passage_id": "c6aa1d9471cd385d590c7759325e471f" }, { "passage": "ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከአንድ ሚሊየን በላይ የዓለምን ሕዝብ ያጠቃው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ያልገባበት ቤት፣ ያላንኳኳው በር የለም። ከዓለም ታላላቅ አገራት መሪዎች እስከ ተራው ሕዝብ፣ ከዝነኛ ሰዎች እስከ ሕፃናትና አዛውንት ድረስ የዚህ አስከፊ ወረርሽኝ ተጠቂ ሆነዋል። ቫይረሱን ለመቋቋም በሽታን የመመከት ከፍተኛ አቅም ያላቸው የስፖርቱ ዓለም ሰዎች ሳይቀሩ በዚህ ወረርሽኝ ተለክፈዋል፣ ሕይወታቸውን ያጡም ጥቂት አይደሉም። የስፖርት ቤተሰቡ በቫይረሱ ስርጭት ስጋት የዓለም ታላላቅ የስፖርት መድረኮች ተቆልፈውበት ሁነኛ የመዝናኛ አማራጩን አጥቶ በየቤቱ ቆዝሟል። የስፖርቱ ዓለም ታላላቅ ከዋክብትም ረብጣ ገንዘብና ዝናቸው ከደጃፋቸው እንዲወጡ አቅም አልሆናቸውም። \nየኮሮና ቫይረስ በስፖርቱ ዓለምና በስፖርት ቤተሰቡ የሚያሳድረው አሉታዊ ተፅዕኖ በሳምንቱ አጋማሽ ወደ ሃዘን የቀየረ አጋጣሚ ፈጥሯል። ፈረንሳዊው እውቅ የስፖርት ጋዜጠኛ ፔፕ ዲዉፍ ባለፈው ረቡዕ በኮሮና ቫይረስ ምክኒያት ሴኔጋል መዲና ዳካር ውስጥ በስልሳ ስምንት ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የመለየቱ ዜና ተሰምቷል። ይህም በመላው ሴኔጋልና አፍሪካ እንዲሁም ፈረንሳይ ትልቅ የስፖርቱ ዓለም አሳዛኝ ክስተት ሆኗል። \nትውልዱን በቻድ አቢቼ ያደረገው ዲዉፍ ከሴኔጋላዊ ቤተሰቦች የተገኘ ሲሆን የቻድ፣ ሴኔጋልና ፈረንሳይ ዜግነት አለው። ገና የአስራ ሰባት ዓመት ወጣት እያለ ለብቻው ወደ ፈረንሳይ ያቀናው\n ዲዉፍ የፖለቲካል ሳይንስ ካጠና በኋላ የፈረንሳዩ ክለብ ኦሊምፒክ ደ ማርሴል ጋዜጣ ላይ ፅሁፎችን በማበርከት ነበር ወደ ስፖርት ጋዜጠኝነት ሕይወት የገባው። ይህም በኋላ ላይ የተጫዋቾች ወኪል ሆኖ ለመስራቱ ትልቅ በር የከፈተለት አጋጣሚ እንደነበር የታሪኩ ፀሐፊዎች ይናገራሉ። ዲዉፍ የተጫዋቾች ወኪልነት ስራውን የጀመረው የቀድሞውን ፈረንሳዊ ተከላካይ ባሲል ቦሊ እንዲሁም ካሜሩናዊው ግብጠባቂ ጆሴፍ አንቶኒ ቤልን ወደ ማርሴል ክለብ በማምጣት ሲሆን በሂደት ዊሊያም ጋላስ፣ ሳሚር ናስሪና ሌሎችም እውቅ ተጫዋቾችን በደንበኝነት ይዞ ወኪል በመሆን አገልግሏል። በተለይም ኮትዲቯራዊው ኮከብ ዲዲየር ድሮግባ እኤአ ከ2003 እስከ 2004 በማርሴል ቆይታው ወቅት ወኪሉ በመሆን የተሳካ ጊዜ እንደነበረው ይጠቀሳል። \nይህም በእርግር ኳስ ውስጥ የነበረው የነቃ ተሳትፎ እኤአ 2005 ላይ የማርሴል ክለብ ፕሬዚዳንት እስከ መሆን አድርሶታል። ዲዉፍ በአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች የሚሳተፍ ክለብ ፕሬዚዳንት ሲሆን በታሪክ የመጀመሪያው ጥቁር ሆኖ ይነሳል። ዲዉፍ የማርሴል ክለብ ፕሬዚዳንት ሆኖ ሲያገለግል ክለቡ በፈረንሳይ የመጀመሪያው ሊግ ሁለት ጊዜ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ ትልቅ ሚና ነበረው። እኤአ 2009 ላይም ዲዉፍ አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሾን ወደ ማርሴል በማምጣት ክለቡ የሊጉን ዋንጫ እንዲያነሳ አድርጓል። ይህም ክብር ክለቡ ከአስራ ስምንት ዓመታት በኋላ ያጣጣመው ሆኖ ተመዝግቧል። አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሾ ባለፈው የሩሲያ ዓለም ዋንጫ ፈረንሳይ ከሃያ ዓመታት በኋላ ስታሸንፍ የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ እንደነበሩ አይዘነጋም። ከዚህ\n ድል በኋላ ከክለቡ ፕሬዚዳንትነት የለቀቀው ዲዉፍ የፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበርን መርቷል። እኤአ 2009 ላይ በፊፋ ጠቅላላ ጉባዔ ዙሪክ ላይ ተገኝቶ በፈረንሳይ እግር ኳስ ደረጃና በአጠቃላይ እግር ኳስ ውስጥ ስላለው ዘረኝነት ያደረገው ንግግር በታሪኩ ይጠቀስለታል። \nዲዉፍ በአውሮፓ እግር ኳስ ውስጥ አሳሳቢ ስለሆነው የዘረኝነት ጉዳይ ጥቁሮች ሰለባ እንዳይሆኑ በጠንካራ ቃላት በዓለም ሕዝብ ፊት ቆሞ በመሟገት ይታወቃል። በስፖርት ጋዜጠኝነት ሕይወቱም ብዙዎችን በማንቃትና ጠንካራ ስራዎችን በማቅረብ የተጨበጨበለት መሆኑን በርካቶች ይመሰክሩለታል። \nበዚህ ወቅት ዓለምን እያስጨነቀ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ተይዞ የነበረው ዲዉፍ በቤተሰቦቹ አገር ሴኔጋል እርዳታ እየተደረገለት የቆየ ሲሆን ለተሻለ ሕክምና ወደ ፈረንሳይ ለማቅናት በተዘጋጀበት ወቅት ሕይወቱ ማለፉ ተዘግቧል። ይህም በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ በሴኔጋል የተመዘገበ የመጀመሪያው የሞት ዜና ሆኗል። ይህንንም ተከትሎ በርካታ የእግር ኳሱ ዓለም ከዋክብቶች በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን ሃዘናቸውን እየገለፁ ይገኛሉ። \nዲዉፍ ድንቅ ታሪክ የሰራለት ማርሴል ክለብ በትዊተር ገፁ ‹‹ፔፕ ሁል ጊዜም በማርሴል ልብ ውስጥ ይኖራል፣ የማርሴል የምን ጊዜም ታሪካዊ ሰው ነው›› በማለት ሃዘኑን ገልጿል። የፕሮፌሽል ተጫዋቾች ማህበር በበኩሉ ‹‹ጋዜጠኛ፣ወኪልና የቀድሞ የማርሴል ፕሬዚዳንት ፔፕ ዲዉፍ ሕይወቱን ሙሉ እግር ኳስን ሲያገለግል የኖረ ሰው ነው›› በማለት አስታውሶ ሃዘኑን ገልጿል። ፈረንሳዊው የቀድሞ የሊቨርፑል አጥቂ ጅብሪል ሲሴ ዲዉፍ የማርሴል ፕሬዚዳንት እያለ ለክለቡ ተጫውቷል።‹‹የፈረንሳይ እግር ኳስ ዛሬ ድንቅ ሰው አጥቷል›› በማለት ሲሴ የተሰማውን ሃዘን በትዊተር ገፁ አስፍሯል። ሌላኛው ፈረንሳዊ የማንቸስተር ሲቲ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ቤንጃሚን ሜንዲ በበኩሉ ‹‹ድንቅ የክለብ ፕሬዚዳንት ነው፣ ከዚያም በላይ ሁል ጊዜ ለማርሴል እሴቶች የሚጨነቅ ትልቅ ሰው ነው›› በማለት ተናግሯል።\nአዲስ ዘመን መጋቢት 27/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "1b08f73865713f1e30bc30dc44f23f87" }, { "passage": "እግር ኳስ በመዝናኛነቱ እንዲቀጥል ሰላማዊ የውድድር መድረክ መፈጠሩ የግድ ነው። ስኬታማ ሊግ ለመመልከት ደግም ጊዜና ገንዘቡን ወጪ አድርጎ፣ ፀሐይና ብርድ ሳይበግረው፣ተስፋ አስቆራጩን ሰልፍ ተቋቁሞ ስታድየም የሚገኘው የስፖርት ቤተሰብ የአደጋገፍ ስርዓትና ስፖርታዊ ጨዋነት ወሳኝነት አለው።ወጥ የውድድር መርሃ ግብር እጦት፤የዳኝነት ውሳኔ አሰጣጥ ችግር እንዲሁም ደጋፊዎች፤ የተጫዋቾችና የአሰልጣኞች ስፖርታዊ ጨዋነት ምግባር ችግር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መገለጫ መሆን ከጀመሩ ዋል አደር ብለዋል።\nየወንድማማችነትና የመግባባት ምሳሌ የሆነው ንፁህ እግር ኳስ ተብክሏል። የስታድየም ድምቀትና ለእግር ኳሱ ውበት ዋና ተዋናይ የሆኑ ደጋፊዎች የአደጋገፍ ስርአት ተለውጧል።ከስታድየሞቻችን የሚሰሙት ህብረ ዝማሬዎች ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየደበዘዙ በአንፃሩ አፀያፊ ስድቦችና ፀብ አነሳሽ ድርጊቶች ጎልተው ተሰምተዋል፤ታይተዋል።በእግር ኳስ ሁነት ማሸነፍና መሸነፍ ያለና ወደፊትም የሚኖር መሆኑ ተረስቷል።\nይህን ተከትሎ በሚነሱ ግርግሮች ስጋትም ስታድየሞቻችን ለህፃናት፣በእድሜ ለገፉ ሰዎች፣ሴቶችና ለአካል ጉዳተኞች ምቾት የሚነሱ ሆነዋል።አዳዲስ ተመልካችን ለመመልከት እስኪያቅትም የካምቦሎጆው መንደር ለእንግዶቹ በሩን የዘጋ መስሏል።ይሁንና በተለይ ባለፈው ዓመት የፕሪሚየር ሊጉ መገለጫዎች እስኪመስሉ የተስተዋሉና የአገሪቱን እግር ኳስን መቀመቅ የሚከቱ እክሎች በዘንድሮው የሊግ ውድድር እንዳይስተዋሉ ሊጉም ካለፉት ጊዜያት በተሻለ በስፖርታዊ ጨዋናት የታጀበ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ብዙ ደክሟል።\nየኢትዮጵያ እግር ኳስ የፌዴሬሽኑ አዲስ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራ በየክልሉ እየዞሩ ስፖርታዊ ጨዋነትን ማረጋገጥ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ከከተማ አስተዳደሮች ጋር ተወያይተዋል።ክለባትና የደጋፊ ማህበራትም በየፊናቸው የየበኩላቸውን ተወጥተዋል።ክለቦች ተጨዋቾቻቸውን በስነ ምግባርና በእውቀት በማነጽ ረገድ የቤት ስራቸውን እንዲወጡ ተደርጓል። ከሳምንት በፊት በአዳማ ከተማ በስፖርታዊ ጨዋነት ዙሪያ የስፖርት ቤተሰቡን ያሳተፈ ውይይትም ተካሂዶ ነበር ።ይሁንና በስድስተኛው ስምንት የሊጉ መርሃ ግብር ፌዴሬሽኑም ሆነ የስፖርት ቤተሰቡ ጥረት ከንቱ ሆኖ የተለያዩ መድረኮች የተካሄዱ ስብሰባዎችም ፍሬ አልባ ሆነው ታይታል።በእለቱ በቅድሱ ጊዮርጊስና በሃዋሳ ከተማ መካከል ሊካሄድ በነበረው ጨዋታ ቀደም ሲል ለስፖርታዊ ጨዋነት ምክንያት ሆነው የሚቀርቡ ፤የዳኛ ውሳኔ አሰጣጥ ጉድለት፤ አሊያም ዳኞችን ውሳኔ አምኖ አለመቀበል፤ክብር የሚነኩ ዘለፋዎች፣የተጫዋቾችና አሰልጣኞች ለፀብ የሚያነሳሱ ድርጊቶች አልተስተዋሉም።ይልቅስ የስፖርታዊ ጨዋናት ጉድለቱ ጨዋታው ከመጀመሩ ቀድሞ የተከሰተ እንደመሆኑ ሌላ የግጭት መነሾ ተስትውላል። ከጨዋታው መጀመር 25 ደቂቃ ቀድሞ በደጋፊዎች መካከል የተካሄደው አምባጓሮም በርካታ የስፖርት ቤተሰቡን አባላት ለጉዳት ዳርጓል።ክስስቱም ጨዋታውን ለመታዳም ወደ ሜዳ የገቡ ደጋፊዎች ስሜት ክፉኛ አሳዝኗል፣አንገት አስደፍቷል።\nአስር ሰዓት ላይ መጀመር የነበረበት ጨዋታ እስከ ምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ድረስ ቢጠበቅም የኋላ ኋላ በተለይ ሃዋሳ ከተማዋዎች ጨዋታውን ለማካሄድ ባለመፈለጋቸው ሳይካሄድ ቀርቷል።ከብጥብጡ በኋላ ለክስተቱ ዋነኛ ምክንያት ሆኖ የቀረበው፤ በእለቱ ለእንግዳ ደጋፊዎች የተዘጋጀው የመቀመጫ ስፈራ አናሳ ሆኖ መቅረቡ ነው የተባለ ሲሆን፤ይህ ግን ብቻውን ለክስተቱ አሳማኝና በቂ ምክንያት ነበር ብሎ ለመናገር አያስደፍርም። ምክንያቱም የቦታ ጥያቄ ከሆነም በውይይት መፍታት ሲቻል ድንጋይ የሚያወራውር አንዳችም ምክንያት ይኖራል ተበሎ አይታሰብም።\nምንም እንኳን በእለቱ የግጭቱ ቀስቃሽ የሆኑ ደጋፊዎችን በውል መለየት ቢያስችግርና ቅድሚያ ጥፋተኛ የነበረው ማነው የሚለውን አጣርቶ ውሳኔ የሚያሳልፈው የሊግ ኮሚቴው በእለቱ በስታዲየሙ አንድ አቅጣጫ የተስተዋለው ግጭትና በሜዳው ክልል የነበረው ድብድብ በእጅጉ የሚያሳፍ፤ የኢትዮጵያን ፕሪሚየር ሊግም ስርዓቱን የሚያስጠብቅለት እንደሌለ የሚመሰክር ሆኖ ታይቷል።ከሁሉም በላይ በእንግዳ ክለብ ደጋፊዎች በአግባቡ መለየትና ከአደጋ መከላከል የማያስችል አጥር መኖሩም ጉዳቱን ከባድ አድርጎታል።በተለይ የድንጋይ ውርውራውን ተከትሎ ሸሽተው ወደ ሜዳው ክልል በገቡ የሃዋሳ ደጋፊዎችና በቅዱስ ጊዮርጊስ ስትዋርትቶች መካከል የተፈጠረው ግብ ግብ እጅጉን የሚያሳዝን ሆኖ ታይታል።ይሁንና ስታዲየሙን ከአፍ እስከ ገደፉ የሞሉት የፈረሰኞቹ ደጋፊዎች ከምንም በላይ ለስፖርታዊ ጨዋነት በመገዛት ወደ ፀብ አለመመራትና ሜዳ ወደነበሩት የሃዋሳ ደጋፊዎች አለመግባታቸውም በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አሰጥቷቸዋል።\nየስታድየሙን ፀጥታ ለማስከበር የሚመደቡ የፖሊስ ኃይሎች ቀደም ሲል ከነበረው ታሪክ ጋር ሲነፃፃር ችግሮችን በውይይት ከመፍታት ይልቅ ዱላን አማራጭ አድርገው አለመታየታቸው በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አሰጥቷቸዋል።\nበአጠቃላይ አንድ እርምጃ ፈቀቅ ማለት በተሳነው እግር ኳሳችን መሰል ክስተቶች መመልከት የሚቆመው እንዲሁም ሊጉን ስነስርዓት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባቸው የስፖርት ቤተሰቦች ይህኑ ተግባራቸውን በአግባቡ የሚወጡት መቼ እንደሆን ለመረዳት አዳጋች ሆኗል።ከሁሉም በላይ በቅዱስ ጊዮርጊስና በሃዋሳ ከተማ መካከል ሊካሄድ ከነበረው ጨዋታ ቀድሞ የተከሰተው የስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል ግን ሊጉ ዘንድሮም ስርዓቱን የሚያስከብርለት ማጣቱን አሳይቷል።የሊጉን ስነስርዓት ለማስጠበቅ ከስፖርት ቤተሰቡም በላይ ከባድ ኃላፊነት ያለበት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በተለይም ጠንካራ ህግጋትን በማስተላለፍ ረገድ ከባድ የቤት ስራ እንዳለበት አመላክቷል።\nይህን መሰሉ የስታድየም ብጥብጥና ሁከት በጊዜ መፍትሄ ካልተበጀለት፤ ነገሮች ፈራቸውን ሳይለቁ አስቀድሞ ነገሮችን ማስተካከልና መስመር ማስያዝ ካልተቻለ ከዚህም በከፋ ሁኔታ ወደ መቀመቅ መውረዳችን ሳይታለም የተፈታ ይሆናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2011ታምራት ተስፋዬ", "passage_id": "a584f5aadc30450c16fe4134c39a5306" } ]
cfb6ec7f19f03bb1aa48ba58d40e9836
7d2188a7787361b54ce55de5bef8b537
የኮሮና ቫይረስ በተራዘመው ኦሊምፒክም ተፅዕኖው ሊቀጥል ይችላል
የዓለምን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ወደተለየ አቅጣጫ ያዞረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በስፖርቱ ዓለም ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተዘርዝሮ የሚልቅ አይደለም።አንዳች ውድድር በዓለም ላይ እንዳይኖር ከማስገደድ ባለፈ የስፖርቱን ዓለም ሽባ አድርጎታል።ብዙ ታቅዶባቸው፣ ብዙም ተለፍቶባቸው ለዓመታት በዝግጅት ላይ የነበሩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በትልቅ ኪሳራ የሚካሄዱበት ጊዜ እንዲራዘም ግድ ብሏል። ጃፓን ካለፉት ሰባት ዓመታት በላይ ከፍተኛ ዝግጅት ስታደርግበት የቆየችው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በትልቅ ኪሳራ ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረ ታላቅ የስፖርት መድረክ ነው።ይህን ታላቅ የስፖርት መድረክ ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ እየተናነቀውም ቢሆን ለ2021 ለማራዘም ተገዷል።ኦሊምፒኩን ጨምሮ በርካቶቹ ዓለም አቀፍ የስፖርት ውድድሮችና ጉባዔዎች ወደ ቀጣይ ዓመት የተሸጋገሩት የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በቁጥጥር ስር ይውላል በሚል ተስፋ ነው።ይሁን እንጂ በዓለም ላይ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ከተስፋ በስተቀር የቫይረሱ ስርጭት በጊዜ የሚገታ ወይም ፈውስና ክትባት በዚህ ጊዜ እውን ይሆናል የሚያስብል እንዳልሆነ መታዘብ ይቻላል።ይህንን ከግምት ያስገቡት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ኦሊምፒኩ የቫይረሱን ስጋት ለማምለጥ በአስራ ስድስት ወራት ቢራዘምም ከቫይረሱ ተፅዕኖ ሊያመልጥ እንደማይችል ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ማመልከታቸውን አሶሼትድ ፕሬስ አስነብቦታል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩ ወደ 2021 እንዲዘዋወር ውሳኔ ላይ ከደረሰ ወዲህ በቫይረሱ ስጋት በአስተናጋጇ ጃፓን ቶኪዮን ጨምሮ በሰባት ከተሞች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል።ከቀናት በፊት የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱትም በኮሮና ቫይረስ በጃፓን ከስድስት ሺ በላይ ሕዝቦች ሲጠቁ ከመቶ በላይ የሚሆኑት ሕይወታቸውን አጥተዋል።ኦሊምፒኩ እስከሚካሄድ ገና አስራ ስድስት ወራት የቀሩት ቢሆንም የቫይረሱን ስርጭት በነዚህ ጊዜያት በቁጥጥር ስር ማዋል ካልተቻለ ኦሊምፒኩ አሁንም ከስጋት ውጪ ሊሆን እንደማይችል ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።‹‹በዚህ ወቅት ማንም በእርግጠኝነት ቫይረሱን በቁጥጥር ስር አውላለሁ የሚል እምነት የለውም፣ ስለዚህ የተራዘመው ኦሊምፒክ ከቫይረሱ ስጋት ነፃ ይሆናል ብለን ለመናገር ይቸግረናል›› በማለትም ሃሳባቸውን አጠናክረዋል። በቫይረሱ ስጋት ኦሊምፒኩን ከአንድ ዓመት በላይ ለማራዘም እንደተወሰነ ያስታወሱት ስራ አስፈፃሚው፣ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዚህ ወቅት ለተራዘመው ኦሊምፒክ ጠንክሮ ከመዘጋጀት ውጪ ሌላ ነገር ሊያደርግ እንደማይችል አስረድተዋል።ይሁን እንጂ የሰው ልጅ እስከዚያው ቫይረሱን በቁጥጥር ስር ያውላል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልፀዋል።የተራዘመው ኦሊምፒክ ዘንድሮ ሊካሄድ በታቀደበት ተመሳሳይ ወቅት እንዲካሄድ ከመወሰኑ ውጪ በየትኛው ቀን እንደሚካሄድ ቁርጥ ያለ ቀን አልተቀመጠለትም።ይህንንም ለመወሰን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የተለየ አማራጭ እስካሁን እንዳልተመለከተ አስረድተዋል።ከዚህ ይልቅ ኦሊምፒኩን ቀጣይ ዓመት ላይ በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የተቻለውን ሁሉ ጥረት ማድረግ የሚቻልበትን አማራጭ ታሳቢ በማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የቶኪዮ ኦሊምፒክ ወደ ቀጣዩ ዓመት በመራዘሙ ብቻ በጃፓንም ይሁን በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እንደሚያስከትል ቀደም ሲልም ሲነገር ነበር።ይሁን እንጂ ይህ ኪሳራ ምን ያህል እንደሚሆን አሁን ላይ ማስቀመጥ ከባድ እንደሚሆን ስራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል።ነገር ግን ኪሳራው ከባድ እንደሚሆን አስቀምጠዋል። የኦሊምፒክ ውድድሩ ከመራዘሙ አስቀድሞ የወጡ ጥናቶች እንዳመለከቱት ኦሊምፒኩ ከተሰረዘ ወይም ከተራዘመ የጃፓን ጠቅላላ የአገር ውስጥ ገቢዋ 1ነጥብ 4 በመቶ ሊያሽቆለቁል እንደሚችል ተጠቁሟል።ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ የጃፓን መንግስትን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ እንደሚገቡ ቀደም ሲል ተዘግቧል።የጃፓኑ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም ገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ ኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል ተናግሯል።ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለዚህ ኪሳራ ስጋት ሰላሳ ሦስቱንም ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን የገባ ቢሆንም በቂ እንደማይሆን ታምኖበታል።ፕሬዚዳንቱ ቶማስ ባኽም ኦሊምፒኩ መራዘሙን በገለፁበት ወቅት ከባድ ኪሳራ እንደሚኖር በማመን ሁሉም ባለድርሻ አካላት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል፡፡አዲስ ዘመን ሚያዝያ 8/2012
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=30486
[ { "passage": "በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ስጋት ምክንያት ተቋርጠው የቆዩ እንቅስቃሴዎች አሁን ወደ ነበሩበት እየተመለሱ ነው። የአውሮፓ ሊጎችም የውድድር ዓመቱን ካቆመበት በመቀጠል ሂደት ላይ ናቸው። የጀርመን ቡንደስ ሊጋ ከሁሉም ቀድሞ ወደ ውድድር የተመለሰ ሲሆን፤ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ እና የጣሊያን ሴሪ ኤም ከተያዘው የፈረንጆቹ ወር ጥቂት ቀናት በኋላ ካቆሙበት ለመቀጠል ክለቦች ልምምድ ጀምረዋል። የዓለም አትሌቲክስም የዳይመንድ ሊግ ውድድሮችን ለማስጀመር ቀን መቁረጡ ታውቋል። በዚህ ወቅት ሃገራት ከቫይረሱ ቀውስ መጠነኛ ማገገም እንጂ ጥናትና ምርምሩ ያልተጠናቀቀውን ወረርሽኝ ጨርሰው ተቆጣጥረውታል ለማለት አዳጋች እንደሆነባቸው ግልጽ ነው። ዓለም በዚህ ጭንቀት ውስጥ ባለችበት ወቅት ስፖርት ወደነበረበት መመለሱ በጤና ነው? የሚሉ አስተያየቶች ከተለያዩ አቅጣጫዎች እንዲነሱ አድርጓል።\nእርግጥ ነው ክለቦች እንደ ቀድሞው የተጫዋ ቾቻቸውን ሙሉ ደመወዝ መክፈል በማይችሉበት ደረጃ ተቸግረዋል። አትሌቶችም በውድድሮች መሰረዝና መራዘም ምክንያት ገቢ ማግኘት አልቻሉም። በአጠቃላይ በስፖርቱ ዘርፍ የሚሰሩ አካላት በቢሊዮን ለሚቆጠር የገንዘብ ኪሳራ ተዳርገዋል። አሁን ካሉበት በጥቂቱም ቢሆን ለማገገም ደግሞ ውድድሮችን ማካሄድ ይኖርባቸው ይሆናል። ለተመልካች ዝግ የሆኑ ስታዲየሞችና የስፖርት ሜዳዎችም አማራጭ በመሆናቸው ላይ ሁሉም የሊግ አመራሮች ተስማምተዋል። እንዲያም ሆኖ ግን የጤና ባለሙያዎች ዓለም ራስ ምታት ከሆነባት ወረርሽኝ ሳታገግም ወደ ውድድሮች በመመለሳቸው ስጋታቸው ማየሉን አልሸሸጉም።\nበመድሃኒቶች ላይ የማማከር ስራ የሚሰሩት ዶክተር ማሶድ ኤጋ ‹‹ይህ ወቅት አሁንም መገለል የሚያስፈልግበት እንጂ ውድድሮች የሚጀመሩበት ነው ለማለት ያስቸግራል›› ሲሉ ቲአቲ ወርልድ ለተባለ ድረ ገፅ ስጋታቸውን ገልጸዋል። አሁን በጨዋታ ላይ የሚገኘው ቡንደስ ሊጋ ከመንግስት ፈቃድ ያገኘው እያንዳንዱ ክለብ ንጽህናውን በሚገባ እንዲጠብቅ በማሳሰብ ጭምር ነው። ከዚህ ቀደም በእግር ኳስ ማህበሩ ሁለት ዲቪዚዮን ውስጥ የሚጫወቱ 1ሺ724 ተጫዋቾች ላይ በተደረገው ምርመራ 10 የቫይረሱ ተጠቂዎች መገኘታቸውን ዘገባው አስታውሷል። በመሆኑም ንጽህናን ከመጠበቅ ባሻገር እያንዳንዱ ተጫዋች በየዕለቱ መመርመር እንዳለበት ዶክተር ማሶስ ያሳስባሉ። ይህ ካልሆነ ግን ቫይረሱ ድምጹን አጥፍቶ ከአንዱ ተጫዋች ወደሌላው ከዚያም\n ወደ ክለቦች በመዛመት ለመቆጣጠር አደገኛ ሊሆን እንደሚችልም ይጠቁማሉ። \nአሁንም ከተመልካች ውጪ ጨዋታን ማካሄድ አቻ የሌለው አማራጭ መሆኑ በስፖርት ቤተሰቦች ዘንድ ታምኗል። የጤና ባለሙያዎች በአንጻሩ ተመልካቾች ባይኖሩም በስታዲየም አካባቢ ከ100 የሚልቁ ሰዎች መገኘታቸው ከስጋት እንደማያድን ነው የሚያስገነዝቡት። ሊጎች እንዲሁም ክለቦች በበኩላቸው ከገቡበት የኢኮኖሚ ጫና ለመውጣት ባላቸው ብርቱ ፍላጎት ምክንያት የባለሙያዎችን ምክር ችላ እንዳሉ ቀጥለዋል። ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ቀሪዎቹን 92 ጨዋታዎች በማካሄድ የውድድር ዓመቱን ካላጠናቀቀ የ1ነጥብ25 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ የሚያጋጥመው ይሆናል። በመሆኑም በተመረጡ ስታዲየሞች ከደጋፊ ውጪ ጨዋታዎቹን ለማካሄድ ቀናት ብቻ ቀርተዋል፤ ክለቦችም የልምምድ ሜዳዎቻቸውን ከፍተዋል። የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው ጨዋታዎቹን የግድ መቀጠል ቢገባ እንኳን ክለቦች ተጫዋቾቻቸውና ቤተሰቦቻቸው ላይ ሞት ሊከተል እንደሚችል፣ የሚገጥማቸውን ኪሳራ እንዲሁም ካሳን ታሳቢ ማድረግ እንዳለባቸው ያሳስባሉ።\n ሌላው የባለሙያዎች ስጋት የወረርሽኙ ፈጣን ስርጭት ሲሆን፤ በላብ እንዲሁም በግብ ጠባቂዎች ጓንት አማካኝነት የመዛመት እድሉ ሰፊ መሆኑንም ነው ያመላከቱት። ለዚህ ስጋት ምክንያት የሆነው ደግሞ ባለሙያዎቹ ለሚሰጡት ምክር የየክለቡ የጤና ባለሙያዎች ትኩረት እየሰጡ አለመሆናቸውን ነው። ከዚህ ባሻገር ተጫዋቾች በሚገባ በየዕለቱ ምርመራ እያደረጉ እንኳን፤ ደጋፊዎቻቸው ደግሞ ጨዋታን በቴሌቪዥን ለመከታተል አካላዊ ርቀታቸውን ሳይጠብቁ ይሰባሰቡ ይሆናል የሚል መሆኑን ዶክተር ማሶድ ያሰምሩበታል። \nየቡድን ስፖርቶች በባህሪያቸው ለአካላዊ ርቀት የማይመቹ በመሆናቸው እንደየስፖርት ዓይነቱ ውድድሮች ቢቀጥሉ የሚል ምክረ ሃሳብ የሚያቀርቡት ደግሞ በአሜሪካ የኮቪድ 19 ግብረ ኃይል አማካሪ እንዲሁም የብሄራዊ የኢንፌክሽን በሽታዎች ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር አንቶኒ ፉሲ ናቸው። መታሰብ ያለበት ወረርሽኙ እንዴት በቀላሉ ከአፍንጫ ወደ እጅ ከዚያም ወደ ልብስ በመጨረሻም ወደ ሌላ ሰው እንደሚተላለፍ ነው። በመሆኑም ቀጣዩ የስጋት አቅጣጫ ጨዋታዎችና ግጥሚያዎች እንዳይሆኑ መጠንቀቅ አስፈላጊ ነው። \nየዓለምን እግር ኳስ የሚመራው ፊፋ የሕክምና ኮሚቴ ሊቀመንበርና የፊፋ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ዶክተር ሚካኤል ባሮን ሆግ በበኩላቸው ‹‹ዓለም ለእግር ኳስ ውድድሮች ዝግጁ አይደለችም›› ይላሉ። ቤልጂየማዊው ዶክተር ዘ ሰን ከተባለው ድረ ገጽ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ዓለም ለጤና እና ለመድሃኒት ቅድሚያ መስጠት ያለበት ወቅት ላይ መሆኗን ይገልጻሉ። አደጋውን ሲያመለክቱም ‹‹በዚህ ድራማዊ በሆነ ክስተት ውስጥ ኃላፊነት መውሰድ ከባድ ነው። ተጫዋቾች በትክክል ሁለት ሜትሮችን ተራርቀው አይጫወቱም፤ የፊት ጭምብል ማድረግም አይችሉም። በሜዳ እና በመልበሻ ቤትም አብረው ናቸው። በዝግ ስታዲየም ይጫወቱ ቢባልም በሆነ አጋጣሚ ቡድናቸውን ለመደገፍ የገቡ ደጋፊዎች ይገኛሉ። ምርመራውን በየወቅቱ ማድረግ አስፈላጊ ቢሆንም፤ አንድ ሰው በቫይረሱ ተያዘ ማለት ግን ቡድኑን በሙሉ ወደ ለይቶ ማቆያ ማስገባት የግድ ይሆናል። ስለዚህ እግር ኳሱ መታገስ እና የጤና ባለሙያዎችን ምክር መስማት አለበት›› በማለት ያስረዳሉ።\nአዲስ ዘመን ግንቦት 24/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "d1e1d8fb996069b2ab657ee61c2de97b" }, { "passage": "ዓለምን እያሳሰበ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሳቢያ መካሄድ አለመካሄዱ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አምስት ወራት የቀሩት ቢሆንም በርካታ የዓለማችን አገራት በተለያዩ ስፖርቶች የሚያደርጉትን ዝግጅት አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ኢትዮጵያም በዚህ ታላቅ የስፖርት መድረክ በተለይም በአትሌቲክስ ረጅምና መካከለኛ ርቀቶች ውጤታማ እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በቀድሞው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አባዱላ ገመዳ የሚመራ ብሔራዊ የዝግጅት ኮሚቴ በማዋቀር የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ሰንብቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውጤት በሚጠበቅበት የአትሌቲክስ ስፖርት ኢትዮጵያን እንዲወክሉ\nየተመረጡ አትሌቶች ከመጋቢት ሦስት ጀምሮ ወደ ሆቴል ገብተው ዝግጅት እንዲጀምሩ ውሳኔ ላይ መድረሱን ያሳወቀ ሲሆን፣ አትሌቶችና\nአሰልጣኞች ከትናንት ጀምሮ በኦሊምፒክ ኮሚቴ ፅሕፈት ቤት በአካል በመገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሁለት ሳምንት በፊት በኦሊምፒኩ ኢትዮጵያን የሚወክሉ\nአትሌቶችና አሰልጣኞችን መልምሎ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በመካከለኛ ርቀት፣ ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል፣ ረጅም ርቀት፣ ማራቶንና\nርምጃ ውድድሮች አሰልጣኞችና አትሌቶች መመረጣቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት\nበመካከለኛ ርቀት አሰልጣኝ ብርሃኑ መኮንን፣ ሃብታሙ ግርማ፣ ኢሳ ሽቦ እና ጉዲሳ ታሱ በአሰልጣኝነት ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም\nኃይለማሪያም እና ስንታየሁ ካሳሁን ደግሞ በተጠባባቂነት ተይዘዋል፡፡ በ3ሺ ሜትር መሰናክል ደግሞ አሰልጣኝ ተሾመ ከበደ እና ዶክተር\nብዙአየሁ ታረቀኝ ሲመረጡ አሰልጣን ከፍያለው አለሙ ተጠባባቂ ሆነዋል፡፡ አገሪቷ በኦሊምፒክ\nመድረክ በተለይ ውጤታማ በሆነችባቸው የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር ርቀቶችም አራት አሰልጣኞች ተመራጭ ሆነዋል፡፡ አሰልጣኝ ሁሴን ሸቦ፣\nቶሌራ ዲንቃ፣ ንጋቱ ወርቁ እና ኃይሌ እያሱ ሲመረጡ፤ አሰልጣኝ ተፈሪ መኮንን እና በሪሁን ተስፋይ ደግሞ የተጠባባቂነት ስፍራን\nይዘዋል፡፡ በረጅሙ የአትሌቲክስ ውድድር ማራቶን በማናጀር አሰልጣኝነት ስኬታማ የሆኑት አሰልጣኝ ሃጂ አደሎ ከሌላው ስኬታማ አሰልጣኝ\nገመዶ ደደፎ ጋር በመሆን የርቀቱን እንዲመሩም ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኝ ጌታነህ ተሰማ እና ይረፉ ብርሃኑ ደግሞ ተጠባባቂ ሆነው ተይዘዋል፡፡\nየእርምጃ ቡድኑም በሻለቃ ባየ አሰፋ አሰልጣኝነት የሚያመራ ይሆናል፡፡ ውጤት በሚጠበቅበትና\nታሪካዊ ሊሆን እንደሚችል በሚታሰበው የወንዶች ማራቶን ውድድር የ5ና 10ሺ ሜትር የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑና የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ\nአትሌት ቀነኒሳ በቀለ ባለፈው መስከረም በበርሊን ማራቶን ባስመዘገበው ፈጣን ሰዓት መሰረት በዋናነት መመረጡ የሚታወስ ሲሆን ማራቶንን\nጨምሮ በሌሎች ርቀትም ጠንካራ አትሌቶች በቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን ለመወከል ወደ ዝግጅት ይገባሉ፡፡ ከነዚህም መካከል በዶሃው\nቻምፒዮና ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው አትሌት ሞስነት ገረመው 2፡02፡55 የሆነ ሰዓት ባለፈው ለንደን ማራቶን ላይ በማስመዝገቡ በማራቶን\nቡድኑ ውስጥ በሦስተኛ ደረጃ ተመራጭ ሆኗል፡፡ ብርሃኑ ለገሰ በ2፡02፡48 በሁለተኛነት ሲመረጥ የዓለም ሻምፒዮኑ አትሌት ሌሊሳ\nዴሲሳ ከሌሎች አትሌቶች አኳያ ያለው የቅርብ ጊዜ ፈጣን ሰዓት በቡድኑ ሊያካትተው እንደማይችል ይፋ ከተደረገው የእጩዎቹ ዝርዝር\nመረዳት ተችሏል፡፡ በሴቶች ማራቶን የዱባይ ማራቶን አሸናፊዋ ወርቅነሽ ደገፋ 2፡17፡41 ሰዓት በመያዝ በቀዳሚነት ስሟ ሲቀመጥ\nሮዛ ደረጄ 2፡18፡30ና በ2፡18፡34 ሰዓት ሩቲ አጋ በቀዳሚነት ታጭተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በሚጠበቁበት\nየአስር ሺ ሜትር ውድድር የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ አሸናፊው ዮሚፍ ቀጄልቻ 26፡49፡34 በሆነ ሰዓት ሲመረጥ አንዱአምላክ\nበልሁ 26፡53፡15ና በ26፡54፡34 ጀማል ይመር በቀዳሚነት ተመርጠዋል፡፡ በሴቶች የኦሊምፒክ ቻምፒዮኗ አልማዝ አያና ከዓመት\nበላይ በጉዳት ላይ የቆየች ቢሆንም ቀዳሚዋ ተመራጭ መሆን ችላለች፡፡የዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ባለቤቷ ለተሰንበት ግደይና ነፃነት\nጉደታም ከቀዳሚዎቹ እጩዎች መካከል ተካተዋል፡፡ በወንዶች አምስት\nሺ ሜትር በዶሃው የዓለም ሻምፒዮና የወርቅና የብር ሜዳሊያ ያጠለቁት ሙክታር ኢድሪስና ሰለሞን ባረጋ እንዲሁም ሃጎስ ገብረህይወትና\nጥላሁን ሃይሌ በቀዳሚነት ሊመረጡ ችለዋል፡፡ በሴቶች ደግሞ ጸሐይ ገመቹ፣ ሐዊ ፈይሳና ፋንቱ ወርቁ ባስመዘገቡት ሰዓት መሰረት ሊመረጡ\nችለዋል፡፡ኢትዮጵያ በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ከአትሌቲክስ ውድድሮች በተጨማሪ በታሪክ\nለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ተሳታፊ መሆኗን ከሁለት ሳምንት በፊት ማረጋገጥ ችላለች፡፡ በሞሮኮ ራባት ተካሂዶ በነበረው\nየወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት የኦሊምፒክ ማጣሪያ ውድድር ማስተር ሰለሞን ቱፋ በኦሎምፒክ እንደሚወዳደር ማረጋገጡ አይዘነጋም፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 28/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "0144ad88e4be9c873dc8c3c50637e0f6" }, { "passage": "የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለአስራ ስድስት ወራት ከመራዘሙ አስቀድሞ የተፈራው ሊደርስ የሚችለው የፋይናንስ ቀውስና ትልቅ የገንዘብ ኪሳራ መሆኑ ይታወቃል።ኦሊምፒኩ እንደተራዘመ ይፋ ከተደረገም በኋላ የአዘጋጇ አገር ጃፓን መንግስትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሚደርሰው ኪሳራና ተጨማሪ ወጪ ዙሪያ ውዝግብ ውስጥ መግባታቸው አልቀረም።ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ገና ከጅምሩ ኪሳራውን ለማካካስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንደሚጋሩት ተስፋ አድርጎ የነበረ ቢሆንም አሁን አጣብቂኝ ውስጥ እየገባ መሆኑን የሚጠቁሙ መረጃዎች እየወጡ ይገኛል። \nየዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ትልቅ ባለድርሻ አካል የሆነው የዓለም አትሌቲክስ ከተራዘመው ኦሊምፒክ ገቢ ጋር በተያያዘ ድርድር መጀመሩን አሳውቋል።የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንቱ ሴባስቲያን ኮ በዚህ ጉዳይ ላይ ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጋር ንግግር መጀመራቸውን ከትናንት በስቲያ ይፋ አድርገዋል። \nየኢንሳይድ ዘ ጌምስ ሃተታ እንደሚያመለክተውም በርካታ ዓለም አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖች ከተራዘመው ኦሊምፒክ ሊያገኙት የነበረውን ገንዘብ መጠየቅ እንደሚጀምሩ ተረጋግጧል።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩ በመራዘሙ ምክንያት ብቻ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ ገብቶ በሚዳክርበት በዚህ ወቅት ባለድርሻው የሆኑት ታላላቅ ዓለም አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖች ድርሻቸውን ለመጠየቅ ወደ ኋላ አለማለታቸው አስደንጋጭ ዜና ሆኗል። \nአሁን ድርሻውን የጠየቀው የዓለም አትሌቲክስ ትልቁ ባለድርሻ ሲሆን የዓለም ውሃ ዋና እና የዓለም ጅምናስቲክ\n ፌዴሬሽኖች በተከታይነት ትልቅ ድርሻ አላቸው።እነዚህ ፌዴሬሽኖች ብቻ ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ቢያንስ እያንዳንዳቸው አርባ ሚሊዮን ዶላር ድርሻ እንዲሰጣቸው መጠየቃቸው እንደማይቀር ታውቋል።ይህም ኦሊምፒክ በመራዘሙ ብቻ በርካታ ውስብስብ ፈተናዎች ውስጥ ለገባው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖበታል። \n‹‹እንደ አብዛኞቹ የኦሊምፒክ ስፖርቶች የዓለም\n አትሌቲክስም ከኦሊምፒክ የቴሌቪዥን ስርጭት በሚያገኘው ገቢ ላይ ጥገኛ ነው›› ያሉት ሴባስቲያን ኮ ባለፉት አራት ዓመታት ይህን ገቢ ለማግኘት ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመው ይህን ገንዘብ ማግኘት የግድ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ \nየዓለም አቀፉ ብስክሌት ፌዴሬሽን ከኦሊምፒኩ የሚያገኘው ገቢ ለጊዜው ቢራዘምም እስከ 2020 አጋማሽ ገቢ ሊደረግ እንደሚገባ ከወር በፊት ማሳወቁ\n ይታወሳል።የዓለም አቀፉ እጅ ኳስ ፌዴሬሽንም ተመሳሳይ ሃሳብ ያንፀባረቀ ሲሆን ሌሎችም በቀላሉ ሃሳብ እንደማይቀይሩ ይጠበቃል።በተለይም የዓለም አትሌቲክስ ኦሊምፒኩ በመራዘሙ በ2021 በአሜሪካ ዩጂን የሚያካሂደው የዓለም ቻምፒዮና ላይ ተፅዕኖ በመፍጠሩና ጥያቄውን በቀላሉ ወደ ኋላ እንደማይመልሰው ተገምቷል።የ2021 ዩጂን የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከተራዘመው ኦሊምፒክ ጋር የሚካሄድበት ወቅት የሚጋጭ በመሆኑ ወደ 2022 እንዲራዘም መደረጉ ይታወሳል። \nላለፉት ሰባት ዓመታት የበለጠ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የኦሊምፒክ ውድድር መራዘሙ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ማስከተሉ የአዘጋጆቹ ራስ ምታት እንደሚሆን ቀድሞም የታወቀ ነው።ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ የጃፓን መንግስትንም ይሁን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴን በእጅጉ ሊፈትን እንደሚችል በባለሙያዎች አስተያየት ሲሰጥበት የቆየ ሲሆን ሁለቱ አካላት ኪሳራውን ለማካካስ እንደሚደጋገፉና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ለዚህ እንዲዘጋጁ ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። \nየዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲህ አይነት ችግሮች ሲገጥሙት ትልቅ ተቋም እንደመሆኑ የመድህን ዋስትና እንዳለው ይታወቃል።አሁን የገጠመው ግን ካለው የመድህን ዋስትና አቅም በላይ በመሆኑ ነው እዚህ ችግር ውስጥ የተዘፈቀው።ስለዚህ የመድህን ዋስትናው በህጉ መሰረት የሚሸፍነው ኪሳራ እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ ኪሳራውን የሚያካክስበት አንድ ነገር መፈጠሩ የግድ ይሆናል።ይህንን ተጨማሪ ኪሳራ የጃፓን መንግስት እንደሚሸፍን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ቀደም ሲል በተለያዩ አጋጣሚዎች መስማማታቸው ቢገለፅም አሁን የሃሳብ ለውጥ እንዳደረጉ የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ውዝግቦች መነሳታቸው ይታወሳል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 29/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "3a6997daa61fb58690997bfb9f80ec3a" }, { "passage": "ዓለምን በአንድነት እያስጨነቀ የሚገኘው ወቅታዊ ጉዳይ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ወረርሽኝ መሆኑ ይታወቃል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ያስቻለ ፈውስ በዓለም ሳይንቲስቶች፣ የህክምና ጠቢባንም ይሁን በሃያላን አገራት አቅም ማምጣት አልተቻለም። ይህም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ከመለወጥ አንስቶ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በርካታ አሉታዊ ተፅዕኖው እንዲያርፍ አድርጓል። የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ተጽዕኖ እያስተናገደ ከመሆኑ ባሻገር፤ ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጉን መረጃዎች ያመላክታሉ። በወረርሽኙ ሳቢያ ትልልቅ የስፖርት ውድድሮች በመራዘማቸው፣ በመሰረዛቸው እና በመስተጓጐላቸው ኢንዱስትሪውን ከፍተኛ ገቢ እንደሚያሳጣው የተለያዩ ትንበያዎች አመልክተዋል። \nየስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰ ርሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል፡፡ በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በዚህ ዓመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል። የስፖርት እንቅስቃሴን ጨምሮ ሌሎች መደበኛ እንቅስቃሴዎችን በቅርብ ጊዜ ማድረግ የሚቻልበት ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ምልክቶች እየታዩ አለመሆኑ፤ በኢንደስትሪው ላይ የሚደርሰው ቀውስ እንዲያሻቅብ እንደሚያደርገው ተነግሯል። \nየቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ በመሆኑ ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ጠባብ መሆኑ እየተነገረ ባለበት ወቅት ቢቢሲ ከቀናት በፊት ይዞት የወጣው መረጃ ተስፋ ሰጪ ሆኗል። ቢቢሲ ፤ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን\n የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር ሊመለሱ መሆኑን ጽፏል። ከዚህ ውስጥ ደግሞ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ግንባር ቀደም ሊሆን እንደሚችል አስነብቧል። የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ ማሳባቸውን ጠቅሶ፤ በተለይ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማጠናቀቅ ቆርጠው ተነስተዋል ሲል አስነብቧል። \nየዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን መለገሳቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ የተለያዩ ሀገራት ሊጎች እንደ አማራጭ እየቀረበ ይገኛል። በዝግ ስታዲየም ውድድሮችን አማራጭን ወደ ተግባር ለመቀየር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ቆርጠው መነሳታቸውን አስነብቧል። \nየ2020 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር የተቋረጠው። ሊጉ የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ 92 ጨዋታዎች ይቀሩታል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም የውድድር ዘመኑን በመደበኛው መልኩ ለማካሄድ ለመመለስ የሚያስችል ተስፋ የለም። የ2020 ውድድር ዘመን 92 ጨዋታዎችን እንዴት እናጠናቅ በሚለው ዙሪያ የሊጉ ክለቦች የቪድዮ ስብሰባ አድርገዋል። \nበስብሰባው ላይ እንደ ሕክምና ባለሙያዎች ያሉ ያገባቸዋል የተባሉ ሰዎችም ተገኝተው ነበር። ክለቦች ሊጉ በቀላሉ ወደ ውድድር እንደማይመለስ መግባባት ላይ ደርሰዋል። የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ የተቀሩትን ውድድሮች በዝግ ስታዲየም ለማድረግ ከስምምነት መድረሳቸውን ቢቢሲ አስነብቧል። በቪዲዮ ስብሰባ ወቅት «የሊጉ ክለቦች ይህን ለማድረግ ደግሞ ቢያንስ 10 ገለልተኛ ሜዳዎች ያስፈልጋሉ ። ገለልተኛ\n ሜዳዎችን መጠቀም ያስፈለገው ደጋፊዎች ከሜዳ ውጪም ቢሆን እንዳይሰበሰቡ በማሰብ ነው። አልፎም የሚመረጡት ሜዳዎች ከፖሊስና የስፖርት ሜዳዎችን ደህንነት ከሚመረምር አካል ይሁንታ ያገኙ መሆን አለባቸው» መባሉን በዘገባው አስፍሯል። በተጨማሪም ተጫዋቾች በሳምንት ሁለት ጊዜ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ይደርግላቸዋል። በየቀኑ ደግሞ የበሽታው ምልክት ታየባቸው አልታየባቸው የሚለው ይለካል። አልፎም ሜዳዎች በየጊዜው ንፅህናቸው ይጣራል ተብሏል። ተጫዋቾች ከጨዋታ ውጪ ባሉት ጊዜያት ሁሉ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አለባቸው። በውድድር ስፍራዎች ውስጥም ምግብ መብላትም ሆነ ገላን መታጠብ እንዳይችሉ የሚደረግ መሆኑን አመልክቷል። \nየእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማ ጠናቀቅ በገለልተኛ ሜዳ ውድድሮችን ለማድረግ ከስምምነት መድረስ ቢችሉም ከሀገሪቱ መንግስት በኩል የሚኖረውን ተቀባይነት ምን ሊሆን ይችላል ? የሚለው ምላሽ የሚያሻ መሆኑን ዘገባው አንስቷል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት እንዲቆም የተደረገው። የፕሪሚየር ሊጉ አስተዳዳሪ አካል መንግሥት ይሁንታ ሲሰጥ ብቻ ወደ ሜዳ የሚመለስ መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። \nየውድድር አመቱ የቀሩትን 92 ጨዋታዎች ለመጫወት ከስምምነት ቢደርሱም የሀገሪቱ መንግስት ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል የተባለ ነገር አለመኖሩን ዘገባው ጠቅሷል። የዚህ ዓመት ወድድር ይቋረጥ የሚል ሐሳብ ከየትኛውም ክለብ አልመጣም ነበር። በመሆኑም በሁሉም የሊጉ ክለቦች በኩል የተወሰነው ውሳኔ ከመንግስት ድጋፍ የሚያገኝ ከሆነ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መቋጫው በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ሊሆን እንደሚችል ግምቱን አስፍሯል። የእንግሊዝ መንግሥት እንቅስቃሴዎች ቀስ በቀስ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ካደረገ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በዝግ ሜዳ ወደ ውድድር እንደሚመለስ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 27/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "35430572a053b74df06f2fa400489660" }, { "passage": " ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪመየር ሊግ አዲስ ውሳኔ ካላስተላለፈ በቀር በተያዘው ወር መጨረሻ ዳግም ወደ ውድድር ለመመለስ ማቀዱ ይታወቃል፡፡ ይህንን ተከትሎም ማንቸስተር ዩናይትድ ከቀናት በኋላ ልምምድ ይጀምራል:: ታዲያ ተጫዋቾች ከአቋማቸው ላለመውረድ በቤታቸው ሆነው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ ማተኮራቸውን በተለያዩ ጊዜያት ለደጋፊዎቻቸው በሚያጋሩት ተንቀሳቃሽ ምስል ያስመለክታሉ፡፡ ይህ ሁኔታም ቀድሞ ለረጅም ሰዓታት አብረዋቸው ያሳልፉ ለነበሩትና አሁን ግን በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች መልዕክት ለሚለዋወጡት አሰልጣኞች መልካም መሆኑን የቀያዮቹ አሰልጣኝ ኦሊጉነር ሶልሻየር ለኢቭኒንግ ስታንዳርድ ገልጸዋል፡፡ ተጫዋቾች ጤናቸውንና አቋማቸውን በመጠበቁ ሂደት ቤተሰቦቻቸውም እንዲያግዟቸው ጭምር ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተዛመተ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ሳቢያ በርካታ ስፖርታዊ ክንዋኔዎች መታገዳቸውን ተከትሎ ስፖርተኞች ከቤታቸው እንዳይወጡ በመከልከላቸው በቤታቸው ሆነው በተለያዩ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲያሳልፉ አስገድዷቸዋል፡፡ በተንቀሳቃሽ ምስል ሁሉም ከገዳዩ ቫይረስ ራሱን እንዲጠብቅ መልእክት በማስተላለፍና ቫይረሱን ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት ድጋፍ ከማድረግ ባለፈም በቤታቸው ውስጥ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በምን መልኩ እንደሚሰሩ ለሌሎች በማስመልከት ላይም ይገኛሉ፡፡ ከተራዘሙ ውድድሮች መካከል አንዱ ኦሊምፒክ እንደመሆኑ በብሄራዊ ቡድን የተካተቱ ስፖርተኞችም ለአንድ ዓመት በምን መልኩ ብቃታቸውን ጠብቀው መቆየት እንደሚችሉ ልምዳቸውን እያካፈሉ ይገኛሉ፡፡ እንግሊዛዊቷ የሁለት ጊዜ የወርልድ ቴኳንዶ የዓለም ቻምፒዮናዋ ጃዴ ጆንስ ለኦሊምፒኩ በተሻለ ብቃት ለመመለስ በአንድ ዓመት መራዘሙን እንደ መልካም አጋጣሚ የምትመለከተው መሆኑን ትገልጻለች፡፡ ውድድሮች፣ የልምምድ አካዳሚዎች እንዲሁም ጂምናዚየሞች በዚህ ወቅት የተዘጉ ቢሆንም በቤት ውስጥ ልምምድ በማድረግ በስፖርቱ የሶስት ጊዜ ቻምፒዮን በመሆን ታሪክ ለመስራት እየተዘጋጀችም ትገኛለች፡፡ ከዚህም ባሻገር ወቅቱን እንደማገገሚያ ጊዜ በመውሰድ ያለመዘናጋት ልምምድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን እንደገለፀች ዘ ጋርዲያን በዘገባው አስነብቧል፡፡ ሌላኛዋ ዋናተኛም በተመሳሳይ የራሷንና የሌሎችን ህይወት አደጋ ላይ ላለመጣል በቤቷ መሆንን አማራጭ የሌለው መሆኑን ታምናለች፡፡ የአምስት ጊዜ ኦሊምፒክ ቻምፒዮናዋ ኬት ሌዴኪ ከሲኤንኤን ጋር በነበራት ቆይታ ከዓመት በኋላ በሚካሄደው ኦሊምፒክ በደካማ አቋም ላለመሳተፍ ልምምዱን በጎረቤቶቿ መዋኛ ገንዳ ላይ አጠናክራ መቀጠሏን ገልጻለች፡፡ በእርግጥ ለ800 ሜትር ነጻ ዋና ቻምፒዮናዋ ልምምድ የምታደርግበት ገንዳ በቂ ባይሆንም ከአቋሟ ዝንፍ ብላ ላለመገኘት ስትል በልምምድ ላይ ትቆያለች፡፡ አንጋፋው ህንዳዊ የስፖርት ጋዜጠኛ ሮሂት ብሪጅናዝ በበኩላቸው ስፖርቱ ሲመለስ የተሻለ ነገር ማግኘት ይሻል ይላሉ፡፡ በቤት ውስጥ መቆየት አስፈላጊ በሆነበት በዚህ ወቅት ውድድሮች ባይኖሩም ከዚህ ቀደም የተካሄዱ ውድድሮችን እንዲሁም ዘጋቢ ፊልሞችን በመመልከት እያሳለፉ መሆኑን ዘ ስቴር ታይምስ አስነብቧል፡፡ በኢትዮጵያም ከዚህ ቫይረስ መስፋትን ተከትሎ ክለቦች፣ ማሰልጠኛ ማዕከላት እንዲሁም ብሄራዊ ቡድኖች ስፖርተኞቻቸውን እንዲበትኑ ተደርጓል:: ስፖርተኞቹ በቡላቸው ባላቸው አቅም ቫይረሱን ለመቆጣጠር በሚደረገው ርብርብ ከደጋፊዎቻቸውና በተናጥል በመሆን ድጋፍ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን ብቃታቸውን ጠብቀው ለመቆየት ምን እያደረጉ እንደሆነ መረዳት አልተቻለም፡፡ ስፖርተኛ ሁሌም ብቁና ዝግጁ ሆኖ መገኘት ያለበት እንደመሆኑ ከሌሎች ተሞክሮ በመውሰድ ይህንን በቤት ውስጥ የማሳለፍ ወቅት አቅማቸው በቻለ መጠን ዝግጅታቸውን ማከናወን ተገቢ መሆኑን የስፖርት ባለሙያዎችም ይመክራሉ፡፡ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ስፖርተኞች በየግላቸው ጊዜውን እንዲያሳልፉና መመሪያዎችን መከተል እንደሚገባቸው በመግለጫው ጠቁሟል፡፡ በሌላ በኩል በአትሌቲክስ ስፖርት የምትታወቀው ኢትዮጵያ አትሌቶች ከአበረታች መድሃኒት የጸዳ ጊዜ ማሳለፍ እንደሚገባቸው ተመልክቷል፡፡ ብሄራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ጽህፈት ቤት አትሌቶች ሳይዘናጉ ራሳቸውን እንዲጠብቁና በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ያልተገባ ጥቅምን ለማግኘት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የህግ ጥሰት በሚፈጽሙት ላይ የእርምት እርምጅ ይወሰዳል፡፡ ከዚህ ቀደም ይከናወን የነበረው የአትሌቶችን ናሙና የመውሰድና የመመርመር ሂደትም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጽህፈት ቤቱ አሳስቧል፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 24/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "21899956b5d85efbc79462ca38c89e30" } ]
ac0585511f0ccf6ad4702e9fbd7ce30e
519cb5ef8931ca98cc474006d3a8f921
የስፖርት ማህበራት በአዲስ መልክ ይዋቀራሉ
በአንድ አገር ስፖርት እድገትና ውጤታማነት ላይ ሚና ያላቸው በርካታ አካላትን መጥቀስ ቢቻልም፤ ስፖርቱን የሚመሩ አካላት መሰረት መሆናቸው ይታመናል። በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ስፖርቱ የሚመራው በሁለት አካላት ሲሆን፤ ይኸውም ህዝባዊ እና መንግስታዊ ውክልና ባላቸው ነው። ከህዝቡ የተወከሉና ስፖርቱን ለማገዝ በበጎ ፈቃዳቸው እውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ጊዜና ጉልበታቸውን የሚሰጡት አማተር ባለሙያዎች ስፖርትን በበላይነት ይመራሉ። መንግስታዊው አካል ደግሞ በስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ማህበራቱን ለመምራት በተሰጠው ስልጣን መሰረት ስራዎችን ያከናውናል። የመሪው አካል ጥንካሬ እና ድክመት በስፖርቱ እድገት ላይ ከፍተኛ ሚና ያለው እንደመሆኑ የስፖርት ማህበራቱ እንቅስቃሴ ወሳኝ ይሆናል። በኢትዮጵያ ስፖርት ማህበራት ባለው ሁኔታ ጥንካሬውም ሆነ ድክመቱ በአብዛኛው ከህዝባዊው አካል ጋር ማያያዝ የተለመደ ነው። ነገር ግን ከብሄራዊ እስከ ክልሎች ያሉት የስፖርት ማህበራቱ ባለሙያዎች ቅንጅት፣ ከዓለም አቀፍ ሁነት ጋር የመራመድ አቅም፣ ውድድሮችንና ስልጠናዎችን በተያዘላቸው ጊዜና ሁኔታ እንዲካሄዱ ማድረግ፣ ህግና ደንብን ባማከለ መልኩ መንቀሳቀስ እንዲሁም ለስፖርቱ እድገት መታተር ከስራዎቻቸው ጥቂቱ ናቸው። ሆኖም አብዛኛዎቹ ፌዴሬሽኖች ለውጤታማነት በአዲስ ስልትና በተሻለ ሁኔታ ከመቅረብ ይልቅ የበጀት እጥረትንና ሌሎች ጉዳዮችን እንደ እክል ሙጥኝ ማለታቸው ስፖርቱ በዘገምተኛ አካሄድ እንዲገፋ አድርጓል። ይህንን የተመለከተው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም በዚህ ላይ እየሰራ መሆኑን ጠቁሟል። ኮሚሽኑ በቅርቡ አገር አቀፍ የስፖርት ሪፎርም ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀቱ ይታወቃል። በዚህ ላይ ተመስርቶም የስፖርት ዘርፍ የአስር ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተዘጋጅቷል። በሪፎርሙ የተጠቆሙ ጉዳዮች በእቅድ እንዲካተቱ የተደረገ ሲሆን፤ ከእነዚህ መካከል የስፖርት ማህበራትን ማጠናከር አንዱ ነው። በዚህ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ የኮሚሽኑን የቀጣይ አስር ዓመት ስራ ሪፎርሙን መነሻ በማድረግ በተለዩ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን የሚያደርግ መሆኑን ይጠቅሳሉ። ከስራዎቹ መካከል አንዱ ደግሞ የስፖርት ማህበራትን ማጠናከር ነው። ከዚህ አንጻር በእያንዳንዱ ፌዴሬሽን የሱፐርቪዥን ዝርዝር ስራዎች የሚከናወን ይሆናል። ከዚህ በኋላም ኮሚሽኑ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የማህበራቱን ደንቦችና መመሪያዎች የማሻሻል ስራ ይሰራል። በመቀጠልም አገሪቷ ባሏትና ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን የመቀመር ስራዎችን የሚመዝን አዲስ ስታንዳርድ የሚዘጋጅ ይሆናል። በስታንዳርዱ መነሻነትም በብሄራዊ ደረጃ ያለ አንድ ፌዴሬሽን ምን ምን ስራዎችን እንዲያከናውን ይጠበቅበታል እንዲሁም በክልል ደረጃ ያሉ ፌዴሬሽኖች ምን ማሟላት ይገባቸዋል የሚለው በአዲስ መልክ የሚለይ ይሆናል። ኮሚሽኑም የራሱን መስፈርት የሚፈትሽ ሲሆን፤ ፌዴሬሽኖች በስታንዳርዱ መሰረት ለስፖርት ማህበርነት ብቁ ከሆኑ ይመዘገባሉ፣ ካልሆኑ ደግሞ በምዝገባው የማይካተቱ ይሆናል። ፌዴሬሽኖቹን ተከትለው የተቋቋሙ ክለቦችም በተመሳሳይ የማጠናከር ስራም ጎን ለጎን የሚከናወን ይሆናል። ክለቦች ህዝባዊ መሰረት ያላቸው መሆኑ፣ የገቢ ምንጫቸው ከምን እንደሆነ፣ የክለብነት መስፈርቱን አሟልተው ስለመቋቋማቸው እንዲሁም ስላሉበት አጠቃላይ ሁኔታ የመፈተሽ ስራዎችም ይከናወናሉ። በታዳጊዎች የስፖርት ማሰልጠኛ ተቋማትም በተመሳሳይ ፍተሻ በማድረግ በተቀመጠላቸው መስፈርት መሰረት እንዲሰሩ የሚደረግ መሆኑንም ኮሚሽነሩ ያመላክታሉ። በማዘውተሪያ ስፍራዎች ልማት ላይም በተመሳሳይ ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚሰራበትና በሚማርበት አካባቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚደረግበት እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ናቸው በሚለው ላይም ምዘና የሚደረግ ይሆናል። መንግስት በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በማውጣት በሚያስገነባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ ሪፎርሙ ትኩረት ያደርጋል። በተለይ በማዘውተሪያዎች መተዳደሪያ አዋጅ ላይ የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ የሚሰራ ይሆናል። ከዚህ ባሻገር የስራዎቹ አካል በሆኑት ሰራተኞች ላይ ክለሳ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ በተቋሙ ቢፒአር እየተሰራ ይገኛል። በስፖርቱ ልማት ላይ ለውጥ ባለመምጣቱ በሪፎርሙ ዝግጅት ወቅት በተደረገው ጥናት በተለዩ ጉዳዮች ላይ በመንተራስ ወደ ስራ ተገብቷል። መሰል ስራዎችን ማከናወን ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም የስፖርት ማህበራትን በአዲስ መልክ ማደራጀቱ ግን ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ኮሚሽነሩ አስረግጠዋል። ምክትል ኮሚሽነሩ ዱቤ ጂሎ በበኩላቸው ከተወሰኑ ማህበራት ባሻገር አብዛኛዎቹ ያሉት በስም መሆኑን ይገልጻሉ። ዘርፉ በርካታ ችግሮች ያሉበትና ሰፊ ስራን የሚጠይቅ እንደመሆኑ ስትራቴጂካዊ አካሄድ አስፈላጊ ነው። ማህበራት ካልተጠናከሩ፣ የክለቦች አደረጃጀት ላይ ካልተሰራ፣ ታዳጊና ወጣቶችን ላይ ከላይ ጀምሮ የአሰራር ስርዓት ካልተዘረጋ እንዲሁም አካዳሚዎች ላይ የተወሰነ ስራ ሳይከናወን ውድድር ብቻ ማዘጋጀት የትም ሊያደርስ አይችልም። ስራው ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም ማህበራት ራሳቸውን የሚችሉበትን ሁኔታ ከክልል እስከ ዓለም አቀፍ ድረስ የተስተካከለ ግንኙነት ያላቸው እንዲሆኑ የሚሰራ መሆኑን ያብራራሉ።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 7/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=30421
[ { "passage": "የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን የሚመራ የሊግ ኮሚቴ እንደሚቋቋም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።\nለዚህ የሚሆን አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ የተጠናቀቀ ሲሆን፤ ጥር 7 ሁሉም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አንድ ሰው መርጠው በመላክ 16 አባላት ያሉት የኢትዮጵያ የሊግ ኩባንያ (PLC) ለመመስረት የመሰረት ድንጋይ እንደሚጣል የሶከር ኢትዮጵያ መረጃ አመልክቷል።ባለፉት ዓመታት በተደጋጋሚ ክለቦች ራሳቸው ባቋቋሙት የሊግ አስተዳደር መመራት አለባቸው በሚል ለማዋቀር ቢታሰብም በክለቦች መካከል መተማመን በመጥፋቱ ሀሳቡ ሳይሳካ መቅረቱ ይታወቃል። በ2010ዓ.ም ወደ ሥልጣን የመጡት የፌዴሬሽኑ አመራሮችም ክለቦች የራሳቸውን ውድድሮች ራሳቸው መምራት አለባቸው የሚል አቋም ወስደዋል። በዚህም የ2011ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዕጣ የማውጣት ሥነ-ሥርዓት ላይ አደረጃጀቱን እንዲያስፈፅሙ፤ አቶ ሰላሙ በቀለ፤ አቶ አስጨናቂ ለማ እና አቶ ሸረፋ ዴሌቾ መመረጣቸው ይታወቃል።ለወራት የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን የቆየው ኮሚቴውም በቅርቡ ተጨባጭ በሆነ መልኩ ወደ ተግባር ሊገባ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ኮሎኔል አወል አብዱራሂም መግለጻቸውን ዘገባው ይጠቁማል።ኮሎኔል አወል «የሊጉ ባለቤት የሆኑት ክለቦች ሊጉን ሊመሩ ይገባል። ሌላ ሞግዚት አካል መኖር የለበትም። ኮሚቴ ብሎ ዘመናዊ እግርኳስን መጠበቅ አይቻልም። በትርፍ ጊዜ በሰዎች ፍላጎት ላይ ተገድቦ የሚሠራ ሥራ አያዋጣም» ብለዋል።ሊጉ ውድድሮችን ከመምራት ባለፈ የተሻሉ ትልልቅ ሀሳቦች የሚተገበሩበት ዓለም አቀፍ ትኩረት የሚስብ ውድድር መሆን እንዳለበትም ኮሎኔል አወል ገልጸዋል።የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዚዳንት እንዳሉት፤ በፌዴሬሽኑ በኩልም ሊጉ በክለቦች እንዲመራ ፅኑ አቋም አለ፤ ለዚህ የሚሆን አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችም ተጠናቀዋል። በዚህም መሰረት በመጪው ጥር ወር የሊጉ ተሳታፊ ክለቦች 16 አባላት ያሉት የኢትዮጵያ የሊግ ኩባንያ (PLC) ለመመስረት የመሰረት ድንጋይ የሚጣልበት ቀን ይሆናል። ለእግር ኳሱ እድገት ከዚህ ውጪ ሌላ አማራጭ ባለመኖሩ ፌዴሬሽኑ ቆርጦ እንደገባበትም ነው።ሊጉ በአዲስ አካሄድ መከናወን ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የውይይት እና ክርክር አጀንዳ ሆኖ የቆየውና ክለቦች ሊጉን አቋርጠው እስከመውጣት የደረሱበት ራሱን የቻለ የሊግ አስተዳደር በተለያዩ ጊዜያት ይቋቋማል ተብሎ ሲነገር ቢቆይም ክለቦች ሳይስማሙ በልዩነት እየወጡ ሳይሳካ መቅረቱ ይታወሳል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 23/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "646e12cdc906290c590d8ed063643ab7" }, { "passage": "በዓለም አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ የሚገኘውን የሴቶች ቀንን አስመልክቶ፤ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በተያዘው ዓመት ሴት ምክትል ፕሬዚዳንት እንደሚመርጥ አስታውቋል። በዚህም ሴት ስፖርቱን በትልቅ ደረጃ መምራት እንደምትችል በማሳየት ተምሳሌ እንደሚሆንም በድረ-ገጹ ጠቁሟል። እ.አ.አ በ2016 ማህበሩ ሴቶችን በየትኛ ውም የስፖርት ኃላፊነት ቦታዎች ላይ መካተት እንደሚገባቸው በደንቡ ላይ አካትቷል። በዚህም መሰረት ስድስት ሴቶች በማህበሩ ካውንስል እንዲካተቱ ተደርጓል። ይህንን ቁጥር በአንድ ለማሳደግም በተያዘው ዓመት የታቀደ ሲሆን፤ እ.አ.አ በ2023 ደግሞ ቁጥራቸውን አስር ለማድረስ እየተሰራ እንደሚገኝ በዘገባው ተጠቁሟል። በ2027ደግሞ በካውንስሉ የሚገኙ ሴቶች ቁጥር ከወንዶቹ እኩል እንደሚሆን ነው የሚጠበቀው። ማህበሩ የጀመረውን ይህንን እንቅስቃሴ በሁሉም አገራት ፌዴሬሽኖች እንዲሁም በኮን ፌዴሬሽኖች ውስጥ እንዲለመድ በሴቶች ኮሚቴ በኩል እየሰራ ይገኛል። ለምክትል ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውም በእጩነት ብቃት ያላቸው ሴቶችን ማቅረብ ያስፈልጋል። ይህንን አስመልክቶም ያለፉትን 12 ወራት ሴቶችን የአመራርነትና አስተዳደራዊ ስልጠናዎች ለአምስት ኮንፌዴሬሽኖች ተሰጥቷል። ይህንን አስመልክቶም የማህበሩ ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ «የሴቶችን ቀን ምክንያት በማድረግ በማህበሩ ያለውን የጾታ እኩልነት ለማረጋገጥ ያለንን ቁርጠኝነት ስንገልጽ በደስታ ነው። በርካታ ሴቶች ወደ ስፖርት አመራርነት እንዲመጡ ማበረታታት አስፈላጊ ነው። አሰራራችንም ይህንን እንደሚፈልግ መታወቅ አለበት። በምርጫዎች ላይ ለሴቶች እኩል የተሳታፊነት ዕድል ይሰጣል፤ በኃላፊነት እና የተለያዩ እርከኖችም ቦታዎቹም ላይ ሴቶች በእኩል ቦታ እንዲያገኙ እንሳራለን። በእኔ\nእምነት በየትኛውም ተቋም ጠንካራ እንዲሆን የሴቶች ተሳትፎ መጨመር ይገባል» ሲሉም ገልጸዋል። የተቀመጠውን ግብ ማሟላት አስፈላጊ ነገር ይሁን እንጂ በዕውቀት እንዲታገዙ ፕሮግራሞችን መቅረጽ ያስፈልጋል። በዚህም በቴክኒካል ጉዳዮች፣ በህክምና፣ በአሰልጣኝነት እንዲሁም በአመራርነት ማሳተፍ ይቻላል። ይህንን ለማሳካት ደግሞ የየሃገራቱ ፌዴሬሽኖች እንዲሁም ኮንፌዴሬሽኖቹ በትኩረት መስራት እንደሚገባም ፕሬዚዳንቱ አያይዘው ጠቁመዋል። አትሌቲክስን ከሌሎች ስፖርቶች ለየት የሚያደርገው በሁለቱም ጾታዎች አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ርቀቶችና የውድድር ዓይነቶች እንዲሁም የውድድር ቁሳቁሶቹ ተመሳሳይ በመሆናቸው ነው። በሁለቱም\nጾታዎች የሚደረጉት ውድድሮች አንድ ዓይነት ሲሆኑ አሸናፊ የሆኑት አትሌቶችም በእኩል መጠን ተሸላሚዎች ናቸው። ከሜዳ እና መም ባሻገርም ሴቶች በአትሌቲክስ ስፖርት አመራርነት መምጣታቸው እየጨመረ መሆኑም በዘገባው ተጠቁሟል። በማህበሩ ዋና መስሪያ ቤት ካሉት ሠራተኞች መካከል 51በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ፤ ከእነዚህ መካከል 40በመቶ የሚሆኑት በአመራርነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ። የሴቶች ወር መከበሩን ተከትሎም ለሚቀጥሉት ሳምንታት የሴት አትሌቶችን ብቃት እንዲሁም በሜዳ ላይ የነበራቸውን ሁኔታ የሚዳስሱ ዘገባዎች እንደሚወጡም ነው የተጠቆመው።አዲስ\nዘመን መጋቢት 2/2011በብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "cd8ec2dbaff5724cb54c08f9b83b6feb" }, { "passage": "የቅርጫት ኳስ ስፖርት በዓለማችን ላይ ተወዳጅ ከሆኑ ስፖርቶች መካከል\nበቀዳሚነት ይቀመጣል። በአገራችንም ቢሆን የቅርጫት ኳስ ስፖርት ጥሩ እንቅስቃሴ የሚደረግበትና በተለይም በከተሞችና ትምህርት ቤቶች\nአካባቢ በወጣቶች እጅግ ተወዳጅ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ስፖርቱን ለማስፋፋትና ለማሳደግ\nሰፊ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን የቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በአገር አቀፍ ደረጃ እንዲካሄድ ማድረጉ አንዱ\nትልቅ እርምጃ ነው። ከዚህ ጎን ለጎን ስፖርቱ ሰፊ መሰረት ያለው በከተሞች አካባቢ እንደመሆኑ ከሰባት ዓመት በፊት የከተሞች የቅርጫት\nኳስ ውድድርን በየዓመቱ በማካሄድ አበረታች እርምጃ ወስዷል። ፌዴሬሽኑ ዘንድሮም የከተሞችን የቅርጫት ኳስ ውድድር ከኦሮሚያ ስፖርት\nኮሚሽን ጋር በመተባበር በቢሾፍቱ ከተማ እንዲካሄድ አድርጓል። ለአምስት ተከታታይ ቀናት ተካሂዶ ባለፈው አርብ በተጠናቀቀው የከተሞች\nየቅርጫት ኳስ ውድድር በወንዶች መካከል በሚደረገው ፉክክር አዘጋጁ ቢሾፍቱ ከተማን ጨምሮ አዳማ፣ድሬዳዋ፣ሐረሪ፣ቡታጅራ ከተሞች እንዲሁም\nየኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ተሳታፊ ሆነውበታል። በሴቶች መካከል በሚደረገው ፉክክር ግን ባልተጠበቀ መልኩ አሰላ ከተማና\nየኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ብቻ ተሳታፊ ሆነዋል። ከመሐል አገር ራቅ ያሉ ከተሞች በውድድሩ ለመሳተፍ ያሳዩትን ተነሳሽነት\nያህል በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኙ ከተሞች በፉክክሩ ላይ መገኘት አለመቻላቸው ከበጀት እጥረት ጋር ተያይዞ መሆኑ የአገራችን ከተሞች\nለስፖርቱ እየሰጡት ያለውን ትኩረት ትዝብት ላይ የጣለ ነው። አንዳንድ ከተሞች በውድድሩ መሳተፍ ያልቻሉት የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ\nፌዴሬሽን በሚያዘጋጀው የቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ላይ ተሳታፊ በመሆናቸው ሲሆን ራቅ ያሉት ከተሞች በአገራችን ከሚታየው የፀጥታ\nስጋት ጋር በተያያዘ ምክኒያት እንደሆነ የፌዴሬሽኑ የስራ ሂደት ዳይሬክተር አቶ ይመር ሃይሌ ለአዲስ ዘመን ገልፀዋል።በዚህ ውድድር አግራሞትን ካጫሩት ሁነቶች መካከል የአዲስ አበባ ከተማ አፍንጫው ስር በምትገኘው ቢሾፍቱ ከተማ\nበሚካሄድ ውድድር በወንዶችም በሴቶችም መሳተፍ አለመቻሉ ነው። ከተማውን በሁለቱም ፆታ ወክለው ለመወዳደር ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩት\nወጣቶች ከበጀት እጥረት ጋር በተያያዘ መጨረሻ ሰዓት ላይ መሳተፍ እንዳልቻሉ ከተለያዩ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። አዲስ አበባ በየወረዳው እንኳ መሳተፍ የሚያስችል እምቅና ሀይል ያለው መሆኑ ይታወቃል። በየትምህርት ቤቶችና\nበዩኒቨርሲቲ ደረጃ ያለውን የአዲስ አበባ የወጣቶች ቅርጫት ኳስ ፍቅርና አቅምን አሰባስቦ አለመሳተፉ አሳፋሪ ነው። በአገራችን ከሚገኙ\nከተሞች ሁሉ በአፍሪካ ደረጃ ለሚካሄዱ ውድድሮች ጠንካራ ቡድን መገንባት የሚያስችል የቅርጫት ኳስ ፍቅር፣ ጉልበት፣ የፋይናንስና\nየተጫዋቾች አቅም ያለው የአዲስ አበባ ከተማ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ነገር ግን በዚህ የወጣቶችን ችሎታ፣ አቅምና ጉልበት\nለማወቅና ጠንካራ ቡድንን ለመገንባት የሚረዳ የከተሞች ውድድር ላይ አዲስ አበባ ለማሸነፍ ወይም ለመወዳደር ለምን እንዳልቻለ፣ ወይም\nእንዳልፈለገ የሚመለከተው አካል ትኩረት ሰጥቶት ማስተካከል መቻል እንዳለበት የብዙዎች እምነት ነው።አዲስ አበባ የአፍሪካና የኢትዮጵያ መዲና ናት። ወጣቶች፣ ታዳጊዎችና ህጻናት በስፖርት እንዲሳተፉ እድል በመስጠት\nበስነልቦናና በአካል ብቃት የዳበረ ትውልድ መገንባት፣ በአገር ደረጃ ትውልድን ከሱስና አልባሌ ስፍራ ማራቅ ብቻም ሳይሆን ከተሞቻችንንና\nትውልድን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማስቻል ግዴታ እንጂ ውዴታ አይደለም። አዲስ አበባ በበጀት እጥረት በውድድሩ አለመሳተፉ\nየማይመስል ነገር ነው። የከተማ አስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን የቅርጫት ኳስ ውድድሩ ከተጠናቀቀ አንድ ቀን በኋላ እዚያው ቢሾፍቱ ላይ\nበከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ የስፖርት ማህበራት አመራሮችን ለሁለት ቀን ሰብስቦ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሲሰጥ ነበር። በዚህ\nስልጠና ላይ ሰላሳ አምስት ከሚጠጉ የስፖርት ማህበራት የተውጣጡ በመቶዎች የሚቆጠሩ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል። ለዚህም\nየሁለት ቀን ስልጠና ከተማ አስተዳደሩ በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ወጪ ማድረጉ አይቀሬ ነው። ጥያቄው ከተማ አስተዳደሩ በስሩ የሚገኙ\nየስፖርት ማህበራት አመራሮችን አያሰልጥን ሳይሆን ቅድሚያ ለየትኛው መስጠት አለበት ይሆናል። በቅርጫት ኳስ ውድድሩ በሁለቱም ፆታ\nለመሳተፍ ቢበዛ ሃያ የሚሆን ተጫዋችና የልዑካን ቡድን ነው የሚያስፈልገው። የበጀት እጥረት ቢኖር እንኳን ውድድሩ በቅርብ ርቀት\nእንደመካሄዱ ተጫዋቾች እየተመላለሱ እንዲሳተፉ ማድረግ ቀላሉ አማራጭ ነበር። የከተማ አስተዳደሩ የስፖርት ኮሚሽነር አቶ ዮናስ አረጋይ\nበአመራሮቹ ስልጠና ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ‹‹ የአዲስ አበባን የስፖርት ማዕከልነት መልሰን እንገነባለን›› ሲሉ ተደምጠዋል።\nየከተማዋን የስፖርት ማዕከልነትና ገፅታ መገንባት ከተማዋ በስፖርቱ ያላትን ትልቅ አቅም አውጥታ በማሳየት እንደ ቅርጫት ኳስ ውድድሩ\nባሉ አገር አቀፍ መድረኮች ተሳታፊ በመሆንና ቅድሚያ ለሚሰጠው ቅድሚያ በመስጠት እንደሚጀምር ሌሎቹም ቢሆኑ ሊማሩበት ይገባል። አዲስ ዘመን የካቲት 3/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "206c97d4656a506cfc55d25c16194439" }, { "passage": "በብሩክ ገነነ እና ሳሙኤል የሺዋስዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) እ.ኤ.አ በ2006 ዓ.ም በጀርመኗ ሙኒክ ከተማ በጠራዉ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በየሀገራቱ ዉስጥ የሚደረገዉ የእግር ኳስ እንቅስቃሴ የተሻለ ፕሮፌሽናል መልክ እንዲኖረዉ ያግዛል በሚል ያዘጋጀዉን የክለቦች ምዝገባ አሠራር (Club Licensing) ለመጀመርያ ጊዜ ያስተዋዉቃል። በስብሰባዉ የተገኙ የ209ኙ አባል ፌደሬሽን ተወካዮችም በጉዳዩ ዙሪያ ከተወያዩ በኋላ የፊፋን ሐሳብ በመቀበል በየአህጉራቱ የሚገኙ ኮንፌዴሬሽኖች ይህን አሰራር ተቀብለዉ እንዲተገብሩ ዉሳኔ በማሳለፍ ጉባኤዉን አጠናቀቁ። የአዉሮፓ እግር ኳስ ማህበር (UEFA) አዲሱን አሰራር በመተግበር የመጀመሪያዉ ሲሆን በሌሎች ኮንፌዴሬሽኖችም ይህ የክለቦች ምዝገባ አገልግሎት ላይ ዉሏል።ሃገራችን ኢትዮጵያ የምትገኝበት የአፍሪካ እግርኳስ ማህበር (CAF) አሠራሩን ለመተግበር ከ2011 ጀምሮ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን ይህንን ሂደት ለማቀላጠፍም ራሱን የቻለ ኮሚቴ ሰይሟል። ካፍ የአባል ሃገራቱ ክለቦች ለምዝገባ የሚያበቃቸውን መስፈርት እንዲያሟሉ የተለያዩ ቀነ ገደቦችን በተደጋጋሚ ቢያስቀምጥም በክለቦችና አባል ፌዴሬሽኖች ጥያቄ ጊዜዉን ሲያራዘም ቆይቷል። በመጨረሻም እስከ ታህሳስ 31፣ 2016 ዓ.ም. ድረስ በተዘጋጀዉ የክለቦች ምዝገባ ህግ ላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች በማሟላት ከሀገሩ ፌዴሬሽን ፈቃድ (License) ለማግኘት ያልቻለ ክለብ ከ2017 ጀምሮ በሚደረጉ የአፍሪካ ክለብ ዉድድሮች ላይ ተሳታፊ እንደማይሆን በማስታወቁ በ2017ቱ የካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ እና ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ የነበሩ ክለቦች በሙሉ በአሠራሩ ተመዝግበው እውቅና እንዲሰጣቸው አድርጓል። በመቀጠል ደግሞ ካፍ በአባል ሃገራቱ የውስጥ ሊጎች የሚጫወቱ ቡድኖች በሙሉ ክለብ ለመባል የሚያስችላቸውን ዝቅተኛውን መስፈርት በማሟላት ፈቃድ አውጥተው የሚጫወቱበትን አስገዳጅ ስርዓት እንደሚዘረጋ ይጠበቃል።የዛሬው የሶከር-ህግ አምዳችን ትኩረትም በዚህ የክለቦች ምዝገባ አሰራር ምንነት፣ እንዲሁም በክለቦቻችንና በአጠቃላይ በሃገራችን እግር ኳስ እድገት ላይ የሚኖረውን አስተዋፅኦ ላይ ይሆናል።የክለቦች ምዝገባ መመሪያ (Club Licensing Regulation) ምንድን ነው?Lየክለቦች ምዝገባ መመሪያ በዙሪኩ 57ተኛው የፊፋ ጠቅላላ ጉባዔ በመርህ ደረጃ ተቀባይነት ያገኘ ሲሆን የፊፋ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እ.ኤ.አ. ጥቅምት 29, 2007 ዓ.ም. የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ አካል በማድረግ አፅድቆታል፤ ከ2008 ጀምሮም እየተሰራበት ይገኛል። ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ለአባል ፌዴሬሽኖቹ ባሰራጨው ፅሁፍ ላይ ይህንን መመሪያ “፤” ሲል ይገልፀዋል።ይህ ጥራዝ (Document) ክለቦች በሀገርአቀፍ እና ዓለምአቀፍ ውድድሮች እንዲሳተፉ የሚያስችላቸውን ፈቃድ ለማግኘት ማሟላት የሚገባቸውን ዝቅተኛ መስፈርቶች ያስቀምጣል። ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር የፊፋ የክለቦች ምዝገባ መመሪያ (FIFA Club Licensing Regulations) ተብሎ የሚጠራውን ዋንኛ መተዳደሪያ ደንብ ያዘጋጀ ሲሆን የየአህጉራቱ ኮንፌዴሬሽኖች ደግሞ በዚህ ዓለምአቀፍ ዶክመንት ተመርኩዘው የራሳቸውን መመሪያ ማውጣት ይጠበቅባቸዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ጨምሮ የየሃገራቱ ማህበራት ደግሞ ይህን መመሪያ በሀገርአቀፍ ደረጃ እንዲሰራበት ለማድረግ በሚያመች መልኩ በማሻሻል ተግባራዊ ያደርጉታል።ዝቅተኛ መስፈርቶቹ ምንድን ናቸው?ከላይ እንደተገለፀው ክለቦች በሃገርአቀፍ ወይም በኢንተርናሽናል ውድድሮች ላይ ለመሳተፍ እና እንደ አንድ ተቋም ለመስራት እና ለመንቀሳቀስ ይችሉ ዘንድ እውቅና ያስፈልጋቸዋል። ይህም የሚሰጠው አንድ ክለብ ማሟላት አለበት ተብለው የሚታሰቡ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሳካት ሲችል ነው። ቅድመ ሁኔታዎቹ በ5 ዋና ዋና ዘርፎች ውስጥ የሚጠቃለሉ ሲሆኑ እነዚህም ስፖርታዊ፣ የመሰረተ ልማት፣ የሰው ሃይል እና አስተዳደራዊ፣ ህጋዊ እና የፋይናንስ መስፈርቶች ናቸው።ክለቦች ከላይ የተጠቀሱትን ሁኔታዎች ማሟላታቸው በሚገመገምበት ወቅት በሶስት የተከፈሉ A B እና C በሚል የሚጠሩ እርከኖች በጥቅም ላይ ይውላሉ። በA ረድፍ ስር ያሉ ቅድመ ሁኔታዎች የግድ መሟላት ያለባቸው ናቸው። B በአንዳንድ ውድድሮች ላይ ለመሳተፍ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች ሲሆኑ፤ የC ክፍል ውስጥ ያሉ ቅድመ ሁኔታዎች ግን እንዲተገበሩ ግዴታ የሌለባቸው ነገር ግን የሚበረታቱ፤ ወደፊትም ግዴታ ሊሆኑ የሚችሉ “ጥሩ ልምዶች” ናቸው።1) ስፖርታዊ ቅድመ ሁኔታዎችአንድ ክለብ ውጤታማነትን አላማው አድርጎ እንደ መነሳቱ በፕሮፌሽናል ተጫዋቾች መዋቀሩ የግድ ይሆናል። በተለይም በሀገራችን ከፕሮፌሽናልነት ጋር ለረጅም አመታት የሚነገሩ የተዛቡ አመለካከቶች አሉ። ኢትዮጵያዊ ተጫዋቾች ከሀገር እስካልወጡ ድረስ ፕሮፌሽናል አይደሉም የሚሉ አካላት እንደዚህ ላሉት አመለካከቶች መነሻ ናቸው። ነገር ግን የፕሮፌሽናልነት ዓለማቀፋዊ ትርጓሜ በተለይም በእግር ኳሱ ዓለም ለስፖርቱ ሙሉ ጊዜውን ሰጥቶ የሚጫወት እና ለአገልግሎቱም ክፍያ የሚያገኝ ነው።ክለቦች በመዋቅራቸው ስር የታዳጊ እና የሴቶች ቡድንን መያዝ ያስፈልጋቸዋል። ለተጫዋቾቻቸውም ዘመናዊ እና ጥራቱን የጠበቀ የህክምና አገልግሎትም መስጠት አለባቸው።ይህ ክፍል ክለቦች ደረጃቸውን የጠበቁ የወጣቶች አካዳሚ እና የወጣት ተጫዋቾች ማብቂያ ፕሮግራሞች ሊኖራቸው እንደሚገባ ይገልፃል። ይህ ማለት ክለቦች ከ15-21 ዓመት እና ከ10-14 ዓመት ባሉ የእድሜ ክልሎች ውስጥ ቢያንስ አንድ የተሟላ የወጣት ቡድን ይኖራቸዋል ማለት ነው። ክለቦች የወጣት ተጫዋቾቻቸውን እግርኳሳዊ የሆኑ እና ያልሆኑ ትምህርቶች እና የህክምና ወጪዎችን የመሸፈን ግዴታ አለባቸው። ይህ አሠራር ለዋና ቡድኑ የሚመጥኑ ተጫዋቾችን ማፍራት ከማስቻሉ በተጨማሪ ክለቦቹ ያሠለጠኗቸው ከ23 ዓመት በታች ያሉ ተጫዋቾች ባህር ማዶ ወዳሉ ክለቦች የሚዘዋወሩ ከሆነ ከዝውውር ሂሳቡ ድርሻ እንደሚኖራቸው በዚህ መመሪያ ተቀምጧል።2) መሰረተ ልማትአንድ ክለብ ውድድር ለማድረግ የሚያስችለው ደረጃውን የጠበቀ ስቴዲየም ባለቤት መሆን አለበት። ስቴዲየሙ ተመልካቾችን እና የሚዲያ አባላትን በበቂ ሁኔታ ማስተናገድ የሚችል አሰራር ሊኖረው ይገባል። ተጫዋቾቹም ልምምድ መስራት የሚያስችላቸው ደረጃውን የጠበቅ የማሰልጠኛ ቦታ ያስፈልጋቸዋል።የክለብ ስቴዲየም ለተመልካች ምቹ፣ ሳቢ እና ደህንነቱ አስተማማኝ መሆን አለበት። የህክምና ቦታዎች፣ ሱቆች እና ደረጃቸውን የጠበቁ መፀዳጃ ቦታዎችም መሟላት አለባቸው። የስቴዲየሙ መገኛ ለትራንስፖርት አመቺ መሆኑም የግድ ነው። ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ምቹ እና በበቂ ሁኔታ የተደራጀ ስታዲየም ደጋፊዎች የተሟላ እና አዝናኝ የጨዋታ ቀን እንዲያሳልፉ ይረዳል።አንድ ስቴዲየም በጥራቱ መሰረት በተለያዩ እርከኖች ይከፋላል። ተመልካች የመያዝ አቅሙ ፣ የመገኛው አመቺነት ፣ የመብራት (ባውዛ) ጥራት እና የህክምና መስጫ ቦታዎች መለኪያ መስፈርቶቹ ናቸው።ወደ ሀገራችን ሁኔታ ስንመጣ ክለቦች በአብዛኛው የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በበቂ ሁኔታ ያሟላሉ ወይ ብለን ለመጠየቅ እንገደዳለን። ፌደሬሽኑስ ክለቦችን ወደ ውድድር ከማካተቱ በፊት መስፈርቶቹን የመመልከት እና ያለመመልከቱ ነገር ሌላው አሻሚ ጉዳይ ነው። ዘመናዊ እና ህግን መሰረት ያደረገ አሰራር ብቸኛው የስኬት መንገድ ነው። የሚመለከተው አካልም የደንቦቹን ተፈፃሚነት የማረጋገጥ ግዴታ አለበት።3. የሰው ሐይል እና አስተዳደራዊ መስፈርቶችበመሠረታዊነት የአንድ በትክክል ፕሮፌሽናል የሆነ ክለብ ፋይናንስ፣ ማርኬቲንግ፣ መዝናኛ፣ ሚድያ፣ ህግ፣ ሰው ሐይል አስተዳደርን የመሳሰሉ ክፍሎቹ ፕሮፌሽናል በሆኑ እና በየዘርፉ ዕውቀት ባላቸው ሰዎች መመራት አለበት። ይህ መስፈርትም ክለቦች በቂ እውቀት ያላቸው ሰራተኞችን ቀጥተኛ በሆነ ቅጥር ወይንም በአማካሪነት ማሰራት እንዳለባቸው ይገልፃል።4. ህጋዊ መስፈርቶችየህጋዊ መስፈርቶች አላማ በአንድ ውድድር የሚሳተፉ ሁለት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ክለቦች በአንድ አካል ንብረትነት፣ አስተዳደር ወይንም ተፅዕኖ ስር እንዳይሆኑ በማድረግ ውድድሩ ከአሠራር ችግሮች የነፃ እንሆን ማስቻል ነው። በዚህ መመሪያ መሰረትም አንድ ግለሰብ፣ ድርጅት ወይንም የመንግስት አካል ከአንድ በላይ ክለቦችን በባለቤትነት አልያም በአስተዳዳሪነት ሊያንቀሳቅስ አይችልም። ወደ ሐገራችን ስንመጣ ደግሞ ለምሳሌ የክልል መንግስታት በክልሉ ውስጥ የሚገኙ ሁለት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ክለቦችን በቀጥተኛ ባለንብረትነት ወይንም አስተዳዳሪነት መምራት እንደማይችሉ ህጉ ያስቀምጣል።\nከዚህ በተጨማሪ ክለቦች ግልፅ የሆነ የንብረትነት እና አስተዳደር አደረጃጀት ሊኖራቸው እንደሚገባ እንዲሁም እግርኳስ ነክ የሆኑ ክሶች በመደበኛ ፍርድ ቤት እንዳይታዩ የሚከለክለውን ጨምሮ የሚሳተፉበት ውድድር ህጎችን የማክበር ግዴታ አለባቸው።5. የፋይናንስ መስፈርቶችይህ ክፍል ክለቦች ግልፅ እና ተቀባይነት ያለው የፋይናንስ አሠራር መዘርጋት ይገባቸዋል ሲል ቅድመ ሁኔታዎችን ያስቀምጣል። የፋይናንስ አስተዳደርን ዘመናዊ በማድረግና ወጪና ገቢን በአግባቡ መዝግቦ በመያዝ ክለቦች የፋይናንስ መረጋጋትን (Financial Stability) ማምጣት ከመቻላቸውም በላይ ገንዘብ ለጋሾቻቸውን እና የክለቡ ባለቤቶችን ከትችት ማዳን ይችላሉ።በክፍል 2 ፅሁፋችን የክለቦች ምዝገባ እና ፈቃድ አሠጣጥ አሰራር ውስጥ የተካተቱ መስፈርቶች አስፈላጊነትና፤ አሰራሩም ክለቦች፣ ተጫዋቾች እና ደጋፊዎችን ጨምሮ በእግርኳሱ ላሉ ባለድርሻ አካላት የሚኖረውን ጥቅም በጥልቀት የምንመለከት ይሆናል።", "passage_id": "55e31c8fabeac62ec97be63400099fff" }, { "passage": "በኢትዮጵያ\nአንጋፋ ከሆኑ የስፖርት መድረኮች ቀዳሚ እንደሆነ የሚነገርለት የሠራተኛ ስፖርት ነው:: ይህ የስፖርት መድረክ በሠራተኛው መካከል በሚካሄዱ ውድድሮች አገራቸውን በዓለም አቀፍ መድረኮች ወክለው ማስጠራት የቻሉ ስመ ጥርና የስፖርቱ ባለውለታ የሆኑ ስፖርተኞችን ማበርከቱም በውስጡ ያለፉ አንጋፋ ሰዎች ይመሰክሩለታል:: ይሁን እንጂ ይህ የስፖርት መድረክ እንደቀድሞ ዝናውን ይዞ መዝለቅ አልቻለም:: ለአገር\nእንደዋለውና እንዳበረከተው አስተዋፅኦም ሲነገርለት አይስተዋልም:: ይህ የስፖርት መድረክ ቀድሞ የነበረውን ዝና የሚመሰክር በወቅቱ የነበረ ሰው በቀላሉ ማግኘትም ከባድ ነው:: የሠራተኛው ስፖርት ወርቃማ ዘመን ላይ ከነበሩት አንጋፋ ግለሰቦች አንዱ አቶ ብርሃኑ አበራ ናቸው:: አቶ ብርሃኑ በኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) የስፖርት ክፍል ኃላፊ ሆነው ለበርካታ ዓመታት አገልግለዋል:: በ1990 ዓ.ም ከኃላፊነታቸው ከለቁቁ በኋላ የሠራተኛው ስፖርት በሚካሄድባቸው ስፍራዎች አይጠፉም:: የፊታችን ረቡዕ ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ቀን ሲከበር ጅማ ከተማ ላይ በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች አብሮ ይከበራል:: ይህንንም አስመልክቶ የሠራተኛው ስፖርት ድሮና ዘንድሮ ምን አይነት ገፅታ እንዳለው አቶ ብርሃኑ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደሚከተለው ያወጋሉ::የሠራተኛው\nስፖርት አጀማመር የስፖርት እንቅስቃሴ በሠራተኛው መካከል ሲጀመር አብረው የጀመሩት አቶ ብርሃኑ አንጋፋው የስፖርት መድረክ ኢሠማኮ ከመመስረቱ በፊት የኢትዮጵያ ሠራተኞች የስፖርት ማህበር በሚል ይንቀሳቀስ እንደነበር ያስታውሳሉ:: እዚያ ውስጥም የተወሰነ ሠራተኛ በራሱ ተሰባስቦ በስፖርቱ ይንቀሳቀስ እንደነበር:: ኢሠማኮ በዘጠኙ ኢንዱስትሪዎች ተከፋፍሎ ሲመሰረት አቶ ብርሃኑ በፋብሪካ ኢንዱስትሪ ማህበር ውስጥ ነበሩ:: መጀመሪያ የተደራጀውም ይህ እንደነበር ይናገራሉ:: ዘጠኙ ኢንዱስትሪ ማህበራት ከተቋቋሙ በኋላ የስፖርት ማህበር ስለማቋቋም ሲነሳም ለአመራርነት ኮሚቴ ሰዎች ተወክለው ነበር:: ታዲያ\nያኔ እንደ አጋጣሚ አቶ ብርሃኑ የመመረጥ እድሉ ገጠማቸው:: የሠራተኛው ስፖርት በዓል ተብሎ 1970 ዓ.ም ላይ ተከብሮ እንደነበር የሚናገሩት አንጋፋው የሠራተኛ ስፖርት መሪ፣ የላብአደሩ የስፖርት እንቅስቃሴ ከዚያ ጊዜ አንስቶ እየተጠናከረ መምጣቱን ያወሳሉ:: ‹‹1975 ዓ.ም ላይ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ሲቋቋም (የታወቁ የስፖርት ድርጅቶች ነበር ያኔ የሚባለው) አንዱ የሠራተኛው የስፖርት ማህበር ነበር ይላሉ›› በወቅቱም እሱን ጨምሮ ሃምሳ አንድ ክለቦች ተቋቋሙ፣ አሁን የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ሥራ አስኪያጅ የሆነው ሰለሞን በቀለ ነበር አዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን የነበረው:: አሁን ላይ በአገራችን ትልልቅ ስም ያላቸው እነ ቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ያሉ ክለቦችም በዚያን ወቅት ተወዳድረው እንደወጡ ያስታውሳሉ:: ከነዚህም\nበተጨማሪ ወደ አስራ አምስት ክለቦች በወቅቱ የወጡት ከሠራተኛው ነበር:: ይህም ከዚያ በፊት ፈርሶ ለነበረው የአገሪቱ ስፖርት የሠራተኛው ስፖርት መቋቋም ዳግም የአገሪቱን ስፖርት እንዲያንሰራራ ማድረጉንም ይመሰክራሉ::የዚያን ጊዜ ከነበሩ ክለቦች የፈረሱ ቢኖሩም አሁንም ድረስ በአገር አቀፍ ደረጃ ትልቅ ስም ያላቸው ሆነው እንደዘለቁም በማስታወስ የሠራተኛው ስፖርት የነበረውን አስተዋፅኦ ያብራራሉ::የሠራተኛው\nስፖርት ድሮና ዘንድሮ የሠራተኛው ስፖርት በወርቃማ ዘመኑ በበርካታ የስፖርት አይነቶች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ የወከሉ ባለውለታዎችን ማፍራት ችሏል:: በተለይም በሦስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ቻምፒዮን ስትሆን የሠራተኛው ስፖርት ትልቅ አቅም ነበረው:: አቶ ብርሃኑ ያን ዘመን ሲያስታውሱ ‹‹ሁሉም ነገር እንደጊዜው ነው›› ይላሉ:: ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት የነበረው አመራር በስፖርቱ ላይ የሚያረካ ባለመሆኑ የሠራተኛውን ስፖርት ስምና ዝና ይዞ መቀጠል እንዳልቻለም ያብራራሉ:: ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህም ቢሆን የተወሰነ መነቃቃት ቢኖርም ሠራተኛው በስፖርቱ ላይ አልነበረም የሚል እምነት አላቸው:: እንዲያውም አሁን ያሉት አመራሮች እነ ፍሰሃፂዮን ቢያድግልኝ (የኢሠማኮ ስፖርት ኮሚቴ ሰብሳቢ) የተወሰነ እያነቃነቁት መጡ እንጂ ስፖርቱ አልነበረም ማለት እንደሚቻል ይናገራሉ:: አቶ ብርሃኑ በእርሳቸው ዘመን የነበረውን ሰፊ የሠራተኛ ስፖርት እንቅስቃሴ መለስ ብለው ሲያወጉም ‹‹በእኛ ዘመን ስፖርት ለጤንነት፣ ለሰላምና ለምርታማነት በሚል ከዳር እስከ ዳር ይንቀሳቀስ ነበር›› ይላሉ:: ይህ ነገር አሁንም አስፈላጊ መሆኑንም ይጠቁማሉ:: ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ እግር ኳስ አሉ ከሚባሉት አሰልጣኞች መካከል እነ አስራት ኃይሌ፣ ነብሱን ይማርና እነ ስዩም አባተ በእግር ኳስ ላይ ስልጠና እንዲወስዱና ውጭ ድረስ እንዲማሩ ያደረገው ይሄው ቤት መሆኑን የሚናገሩት አቶ ብርሃኑ እነዚህ የቀድሞ ተጫዋቾችና የአሁን አሰልጣኞች እንዳሁኑ ዘመን የገንዘብ ፍቅር እንዳልነበራቸው ይመሰክራሉ:: እነ ትግል ፌሬ፣ ርምጃችንና ሌሎችትላልቅ ክለቦች የወቅቱ የስፖርቱ ወርቃማ ዘመን መገለጫዎች ነበሩ:: እነዚህ ክለቦች ሲመሰረቱ በዚህ መምሪያ ስር እንደነበሩ የሚናገሩት አቶ ብርሃኑ፤ ኋላ ላይ ወደ ኢንዱስትሪያቸው ይመለሱ ተብለው ከተመለሱ በኋላም በጥንካሬያቸው መቀጠላቸውን ያስታውሳሉ:: ‹‹አሁን ላይ እኔ የሚመስለኝ አመራሩ ለሠራተኛው የሰጠው ግምትና አመለካከት ዝቅተኛ ነው:: የሠራተኛው ስፖርት አሁን ላይ እንዲቀዘቅዝ ያደረገውም ይህ ነው፣ ይሄ ቤት ቢጠነክር ከዲሲፕሊን ጋር በተያያዘም ይሁን ከሥራ አጥነት ጋር በተያያዘ ወጣቱ በስፖርቱ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ትልቅ ነበረ›› በማለት የአሁኑን ዘመን የሠራተኛ ስፖርት ይገልፁታል:: የሠራተኛው ስፖርት ቀደም ሲል እንደነበረውአስመራ፣ ሐረር፣ ድሬዳዋ፣ ባህርዳር፣ ጎንደርና ሌሎች አካባቢዎች እንቅስቃሴው ቢጠናከር ወጣቱ ወደ ስፖርቱ እንደሚገባ ጠንካራ እምነት አላቸው:: ወጣቱ ሥራውን እየሠራ ስፖርቱ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ይሆንለታል ብለው ያምናሉ:: በቀድሞው ዘመን እንዳሁኑ ምቾት እንዳልነበረ የሚያስታውሱት አቶ ብርሃኑ ‹‹ወጣቱ የሠራተኛ ክፍል ለስፖርቱና ለማለያው የነበረው ፍቅር ቀላል አልነበረም›› ይላሉ:: ይህም ለብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ሲመረጥ ከጦሩና ከሠራዊቱ ሁለት ወይም ሦስት ተጫዋች ካልሆነ በስተቀር አብዛኛው ከሠራተኛው ቡድን እንዲገኝ ማድረጉን ያስታውሳሉ::የሠራተኛው\nስፖርትና ዓለም አቀፉ የሠራተኛ ቀን አቶ ብርሃኑ ሜይ ዴይን አስመልክቶ በቀድሞው ዘመን ሁሉም ቡድኖች አስቀድመው በየኢንዱስትሪያቸው ጨዋታዎችን እንደሚያደርጉ አይዘነጉትም:: በእርግጥ እንዲህ በዓል ጠብቆ ሳይሆን በየቀኑ ውድድሮች እንደነበሩም ይናገራሉ:: ዘጠኙም ኢንዱስትሪዎች የራሳቸውን ውድድር ካደረጉ በኋላ አሸናፊዎቹ ተለይተው ሜይ ዴይ ላይ ለዋንጫ ጨዋታ ይቀርባሉ:: ከዚህ ውድድር በላይ ግን ብዙ ጊዜ ሜይ ዴይ ይከበር የነበረው ወንጂ ስቴድየም ላይ እንደመሆኑ ድምቀቱ የተለየና የማይረሳ መሆኑን ያስታውሳሉ:: ከስፖርተኛው ጋር አብሮ የሚመጣው ሠራተኛ ቁጥርም የበዓሉ ሌላ ድምቀት እንደነበር አይረሱትም:: ክረምት\nላይም ሠራተኛው ውድድር ያዘጋጅ እንደነበር የሚናገሩት አቶ ብርሃኑ፣ በተለይም ድሬዳዋ በሚዘጋጁት ውድድሮች ከአሥመራ ድረስ እየመጡ የተለያዩ ቡድኖች እንደሚሳተፉ ያስታውሳሉ:: እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሚያዘጋጀው የኢትዮጵያ ዋንጫ የሚባል ነበር:: ከዚያ ውድድር ሁለትና ሦስት ሳምንት ቀደም ብለው የተለያዩ ቡድኖች ወደ ሠራተኛው ውድድር ለመምጣት የማያደርጉት ጥረት አልነበረም፣ ከጎንደር፣ ከጅማ ድረስ ይመጣሉ:: ይህም አዳዲስ ተጫዋቾችን እያዩ ክለቦች ራሳቸውን የሚያጠናክሩበት አጋጣሚ ይፈጥርላቸው እንደነበር አንጋፋው ሰው ይናገራሉ::የሠራተኛው\nስፖርና ስፖርታዊ ጨዋነት የሠራተኛው ስፖርት ከቀድሞ ዝናው ይዞት የቀጠለው ነገር ቢኖር ስፖርታዊ ጨዋነት ነው:: አሁን የሚመሰገንበት ስፖርታዊ ጨዋነትም መሰረቱ ያኔ የወርቃማው ዘመን እንደሆነ አቶ ብርሃኑ እንዲህ በማለት ያስታውሱታል ‹‹በሠራተኛው ስፖርት ወርቃማ ዘመን ሥራና ስፖርት እንጂ ፖለቲካና ሌሎች ነገሮች ውስጥ ጊዜ አይባክንም ነበር። አሁንም\nየሠራተኛው ስፖርት በስፖርታዊ ጨዋነት አይታማም›› አቶ ብርሃኑ ከሠራተኛው ስፖርት ወጣ ብለው በአገራችን እግር ኳስ ስለሚስተዋለው የስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል ካካበቱት ልምድ በመነሳት ሃሳባቸውን ይሰነዝራሉ:: በአንድ ወቅት ለአምስት ዓመት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስኪያጅ ሆነው በሠሩበት ጊዜ የነበረውን ሁኔታ ሲያስታውሱ እንዲህ ይላሉ ‹‹ ያኔ እንዳሁኑ ጠብ ሳይሆን ትልቅ ፍቅር ነበር፣ ሜዳ ላይ ማንም ተጫወተ ማንም የኔ ነው ብሎ የሚደግፈው ስፖርቱ ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ ነው፣ ያኔ አይደለም ተጫዋች ስፖርት የሚወዱ ትላልቅ ባለስልጣናት ከስፖርታዊ ጨዋነት ውጭ አንድም ነገር ቢያደርጉ ስቴድየም እንዳይገቡ ይቀጡ ነበር››::ይህን\nሀሳብ ለማጠናከርም በአንድ ወቅት የገጠማቸውን ያወሳሉ::‹ ጄነራል አበራ አያኔ የሚባሉ ኳስ አፍቃሪ ነበሩ፣ እኚህ ጄነራል አንድ ቀን ስቴድየም ውስጥ ከስፖርታዊ ጨዋነት ውጭ የሆነ ነገር ተናገሩ፣ በዚህም ስቴድየም እንዳይገቡ ታገዱ:: አሁን ይሄ ይደረጋል? እኚህ ጄነራል ቅጣቱን ተቀብለው ስፖርቱን ከመውደዳቸው የተነሳ ካታንጋና ሚስማር ተራ ተደብቀው በመግባት ጨዋታ ይመለከቱ ነበር። ይህን\nየሚያደርጉት ከስፖርቱ ፍቅር የተነሳ እንጂ ለሌላ ነገር አይደለም በሚል እገዳውን በኋላ ላይ አነሳንላቸው» የአገራችን የስፖርታዊ ጨዋነት ችግር አንዱም የስፖርት ጋዜጠኞች እውነት አለመናገራቸው ሲሆን አመራር ላይ ያሉትም ሰዎች ችግር አለባቸው የሚል እምነት አላቸው:: «አንዱ ክለብ ወደ አንዱ ሄዶ መጫወት መፍራት የለበትም» የሚሉት አቶ ብርሃኑ፤ ክለቦች በሜዳቸው እንዳይጫወቱ ማድረግ ነገሩን ማባባስ ነው ይላሉ:: ‹‹በእኛ ጊዜ የስፖርት ምክር ቤት ነበር፣ እንዲህ አይነት ችግር ሲኖር ክለቦች ተሰብስበው ይመክሩ ነበር። አሁን\nእንደዚያ አይነት ነገር ያለ አይመስለኝም። እውነተኛ የስፖርት እንቅስቃሴም አይታየኝም። የውሳኔ ችግር አለ። ተገቢና ተመጣጣኝ ቅጣት ቢኖር ይሄ ሁሉ አይፈጠርም›› በማትም ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ:: ወገንተኝነታችን ለስፖርቱ እንጂ ለሌላ ነገር መሆን የለበትም። የስፖርቱን ሕግ ማወቅ በስፖርቱ ሕግ መቅጣት ትኩረት ሊደረግበት እንደሚገባም ምክረ ሃሳባቸውን ይለግሳሉ::የሠራተኛው\nስፖርት ዕጣ ፋንታ ኢትዮጵያ ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር በምታደርገው ሽግግር ውስጥ በርካታ ኢንዱስትሪዎች የመቋቋም ዕድል አላቸው ተብሎ ይታመናል:: በዚህ አጋጣሚም ወጣቶች በብዛት የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ሊያደርጋቸው ይችላል:: ያም ማለት አብዛኛው የሠራተኛ ክፍል ወጣት ሲሆን ከስፖርቱ ጋር ለማቆራኘት መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል:: ይሄን አጣጥሞ መሄድ ትልቁ የቤት ሥራ ነው:: አቶ ብርሃኑ ከያኔው ይልቅ አሁን ኢንዱስትሪዎች ተበራክተዋል ሰፊ እንቅስቃሴም እንዳለ የታዘቡትን ይናገራሉ:: በዚህ ውስጥ ሠራተኛና አሰሪውን አንድ ማድረግና መያዝ የሚቻለውም በስፖርቱ አማካኝነት መሆን እንደሚገባው ያብራራሉ::‹‹ይህን ስናደርግ ስራውም ጥሩ ይሠራል፣ አሰሪውም ከሠራተኛው ጋር በስፖርቱ ምክንያት ይቀራረባል። ቤተሰባዊ ስሜት መፍጠር ይቻላል›› ይላሉ። በዚህ አጋጣሚ ወደ ስፖርት ማህበሩ ያልገባ ድርጅት ካለ ቆም ብሎ ማሰብ እንዳለበት አፅኖት ሰጥተው ይናገራሉ:: ሠራተኛውን በስፖርት ማደራጀት ለጤንነት፣ ለአንድነትና ለስነ ምግባር ቁልፍ ፋይዳ አለው ‹‹ሠራተኛው ዝም ብሏል፣ ይህ ዝምታ ደግሞ ጥሩ አይደለም፣ አንዳንዴ ሠራተኛው በስፖርት ሲደራጅ ቅር የሚለው ይኖራል። የሚያስፈልገው ግን ሠራተኛውን በስፖርቱ በቀላሉ ማደራጀት ›› መፍትሄ መሆኑን ያስቀምጣሉ:: የሠራተኛው ስፖርት አሁንም ጠንካራ ስራ ከታከለበት እንደቀድሞው በእግር ኳስ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ስፖርቶች ለብሔራዊ ቡድን ሊመረጡ የሚችሉ ሠራተኞችን የማፍራት ዕድል አለው:: ኢሰማኮ\nየጀመረውን የማነቃቃት ሥራ አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል:: አሁን በአብዛኛው የሠራተኛው ክፍል ወጣት ነው፤ የበለጠ መቅረብና ማጠናከር ያስፈልጋል፤ ይቺ አገር በሌላት የውጭ ምንዛሬ ተጠባባቂ ወንበር የሚያሞቅ ተጫዋች ከውጭ ክለቦቻችን ማምጣት የለባቸውም የሚል አቋም አላቸው። ክለቦች ታዳጊዎችን ማየት ቢከብዳቸው ከሠራተኛው ስፖርት ዞር ብለው መመልከት እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባ በመግለፅም ሃሳባቸውን ይቋጫሉ::አዲስ ዘመን ሚያዝያ 19/2011ቦጋለ\nአበበ", "passage_id": "fa2bc115d10fe05d6f7aae71721650d0" } ]
65a46bf6c1cdc3d81fee88ecfb4f4608
7a1582433eb029d6859854d300b9a4f9
የእንቁጣጣሽ ትውስታ
 የዘንድሮው እንቁጣጣሽ በጣም አስደሳች ነበር። አበቦቼን ሁሉ ሰጥቼ ጨረስኩ። ጎረቤቶቻችን ብዙ ሽልንጎች፣ ከርኮች፣ ዲናሬዎች ሰጥተውኛል። የፍራንኩ ብዛት ቁጥሩን አሳሳተኝ። ያም ሆነ ይህ ብዙ ገንዘብ አግኝቻለሁ። ያሰብኩትን ሁሉ እንደምገዛ እርግጠኛ ሆንኩኝ። በድንቡሎ አራት ከገዛሁት ደስታ ከረሜላ አንዷን ከመጠቅለያዋ ፈትቼ እየመጠጥኩ እማዬን ሂሳብ እንድናደርግ ጠየቅኳት። «መለዮህንና ማሊያህን እሚገዛልህ አምስት ሽልንግ አለህ» አለችኝ። ተደሰትኩ። (ዳቦ ብላ ብለው እማማ ሸጊቱ ባያስቀምጡኝ ኖሮ ብዙ እሸቅል ነበር) እቤት ቁጭ ብዬ እማዬ ጠብሳ የሰጠችኝን ስጋ እየበላሁ የአንዳንዶቹ ጎረቤቶቻችን ሁኔታ ትውስ አለኝ። አንድ ዓይናው አባባ አጋፋሪ ዓይናቸውን አፍጥጠው አበባዎቹን አንድ በአንድ «ይሄ ማን መሆኑ ነው?» «እመቤታችን ከጌታችን ጋር ነች!» አልኳቸው። መለዮአቸውን ሲያወልቁት ጸሃይ አርፎበት የማያውቀው መላጣ አናታቸው ነጭ ሆኖ ያብለጨልጫል። «ይሄ ጌታችን መሆኑ ነው? ኧረ ልጅ ሳይሆን ትልቅ ሰው ነው እሚመስለው! አስተያየቱስ ቢሆን? ኤድያ! ይሄ አላማረኝም ይቀየርልኝ። ቅዱስ ሚካኤል ጎራዴውን መዞ ሳጥናኤልን ሲቀጣ የሚያሳየውን አበባ ሰጠኋቸው። «ምነው ሰይፉን ጎራዴ አስመሰልከው?» «ጎራዴና ሰይፍ አንድ አይደለም?» «ዝም በል! ጎራዴና ሰይፍ አንድ ነው ይለኛል? ‘ልጅ ለእናቷ ምጥ አስተማረች’ እሺ ይሁንልህ፣ ደግሞስ ሺ በክንፉ ሺ ባክናፉ የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል አንድ ብቻውን በሳጥናኤል ላይ ዘምቶ ሳልከው? አይ የልጅ ነገር! እስኪ ሌላውን አሳየኝ።» የቅዱስ ገብርኤልን ስሰጣቸው አፍጥጠው ሲያዩት ዓይናቸው እንደዓሳ ዓይን ቅንድብ አልባ ሆነ። ትንሽ ፈገግ ብለው የምስራች ነጋሪው ኃያሉ ቅዱስ ገብርኤል ምነው በእሳት ላይ መራመዱን፣ በሚንተገተግ እቶን ላይ ማዝገሙን ገደፍከው?» ብለው ሁሉም ስዕሎች ላይ አቃቂር አውጥተው በገንቦ አበባ የተደረደረበትን ስዕል መረጡ። ራስጌያቸው ካስቀመጡ ዝርዝር ፍራንክ ከርክ አንስተው ሰጡኝ «እድግ በል ልጄ! የሰለሞንን ጥበብ፣ የማቱሳላን እድሜ፣ የኢዮብን ትዕግስት እርሱ አንድዬ ይስጥህ! እናትና አባትህን ጧሪና ቀባሪ ያድርግህ» ብለው መርቀውኝ «ያ አባትህ እንዴት አደረ?» «አንበሳው ሲያገሳ እርሱ ነው የነገረኝ።» «መናገር ጀመረ? ለእርሱ ለአንድዬ ምን ይሳነዋል?አይዞህ እየተሻለው ነው» ብለውኝ ወጣሁ። ለከርሞው ለአበባ አጋፋሪ አበባ እምሰጣቸው መጨረሻ ላይ ነው ብዬ እየዛትኩ ወደ ቤቴ ተመለስኩ። እቤቴ ስገባ የስጋ ጥብስ ሽታ አወደኝ። «ስጋ ከየት አመጣሽ?» «እድሜ ላንተ! አንተ ነህ የገዛህልን» «አበባ ሰጥቼ ባመጣሁት ፍራንክ?» «ታዲያ! እግዚአብሄር ውለታህን ይክፈልህ። በአምስት ሽልንግ ግማሽ መደብ ከማርገጃ ገዝቼ መጣሁ። አሁን ደግሞ ቡና አፈላና ቤታችን ዓመት በዓል ዓመት በዓል ይሸታል።» ኩራት ተሰማኝ። «ግን ከማሊያዬና መለዮዬ መግዣ ፍራንክ ላይ ወሰድሽ?» «በፍጹም! ከእርሱማ አልነካብህም።» ተደሰትኩ። ብር ከስሙኒን ሰጥታኝ ከጉልት ሄጄ መለዮዬን ከእነመነጽሩ እንድገዛ ጠየቅኳት። «ያታልሉሃል» ብላ እምቢ አለችኝ። በዚህ ስንጨቃጨቅ የክርስትና እናቴ እማማ ቦጋለች አንድ በዳንቴል የተሸፈነ ሳህን ይዘው ገቡና «ምንድነው?» ኮስተር ብለው ጠየቁኝ። ነገርኳቸው «ስጪው፣ ጓደኞቹ ውጪ አሉ ያጋዙታል» ሲሉ ፈጥኜ ወጥቼ እኔ ያሰብኳትን ባለመነጽሩን ባርኔጣ ያደረገውን ሲሳይ ጎቢጥን ጠራሁት። አንድ ዓይና መነጽሩን ዛሬ ቀይሮታል።«ና! ባለመነጽሩን ኮፍያህን ለእማዬ ግባና አሳያት!» «እሺ» አለና እየዘነጠ ከፊት ለፊቴ ተራመደ። እናቴን በዚያ ፈጣን ምላሱ አሳመናትና ብር ከስሙኒውን ተቀብለን ወደ ጉልት ሄድን። «የበግ ቆዳ ያለው?!» እየጮኸ ይለፈልፋል ነጋዴው። «የዶሮ ቆዳ ያለው!» አብረውት ይጮኻሉ የሰፈሩ ልጆች። ነጋዴው ጸጥ ብሏቸው ስራውን እየለፈፈ አለፈ። ከገበያ ስንመለስ የሰፈር ልጆች እኛ ቤት አበባየሆይ ይጨፍራሉ። አስናቀች በድርብ ጥርሷ እየሳቀች ከበሮ ትመታለች። መሰረት፣ ሰብለ፣ ፋንቲሽ፣ ጸሃይ፣ አሰገደች፣ ሃዋ፣… እያጨበጨቡ ይቀበሏታል። የካፊያው ጭቃ ከቤት ቤት ሲዞሩ ጫማቸው ላይ ክፈፍ ሰርቷል። ሸራ ጫማ፣ ኮንጎ ጫማ፣ ባዶ እግር ይታየኛል። የሃገር ባህል ልብስ፣ ሻማ፣ ሽንሽን ለብሰው ዘንጠዋል። እማዬ ስሙኒ ሰጠቻቸው። ከብረው ይቆዩን ከብረው በዓመት ወንድ ልጅ ወልደው ሰላሳ ጥጆች አስረው … ከብረው ይቆዩን ከብረው በመነፅሬ ሳያቸው አረንጓዴ ይመስላሉ። ጎረቤታችን እማማ በለጡ ቤት እየጨፈሩ ሲሄዱ እኔ ወደ ጓደኞቼ ሄድኩኝ። ቀጢሳው ፊኛ ይነፋል፣ ተረፈ ገልጆ ሆዱን እያባበሰ ስለበላው ምግብ ደስ እያለው ያወራል፣ ጎቢጥ መነጽሩን አስሬ እያስተካከለ ሲያድግ ስፖርተኛ እንደሚሆን ያወራል፣ ሴምላል ከረሜላውን ቆርጥሞ ያከፋፍለዋል፣ ሻቃ ስለሚገዛው ባለ ብር ኳስ ያወራል፣ ይጥና ትምህርት ቤት ሲጋባ ስለሚገዛቸው ደብተሮች፣ እርሳስና ላጲስ ላውራ እያለ ይወተውታል፣… … አለሚቱ አንጎሏ አበባዬን ተቀብለው ፍራንኬን ሳይሰጡኝ ብዙ አመላለሱኝ። እንደዋዛ ጎራ እያልኩ በሌላ ጉዳይ በበራቸው የማልፍ እየመሰልኩ ታየኋቸው። እርሳቸው ግን ከእነመፈጠሬም የረሱኝ መሰሉ። በመጨረሻም እኔም የማላውቃቸው፣ እነርሱም የማይሰጡን ሆነን እንደተፋጠጥን፣ እንቁጣጣሽ አለፈ። በማግስቱ በራቸው አጠገብ ከጓደኞቼ ጋር ስንጫወት ጠሩኝና ስሙኒ ሰጡኝ። ድካሜን ቋንቋ አልባ ውትወታዬን ሁሉ ረሳሁት። ለነገ «ሙቪ» መግቢያ ቼላ ኖረኛ!!! (ዘነበ ወላ፥ ልጅነት)አዲስ ዘመን መስከረም 5/2012
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=18098
[ { "passage": "በአጋጣሚም\nይሁን ታስቦበት … ግንቦት በኢትዮጵያ ታሪክ በርካታ ድርጊቶች የተፈጸሙበት ወር ነው። ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ታዋቂ ልጆቿን ወልዳለች፤ ወደማይቀረው ዓለምም ሸኝታለች፤ መሪዎቿን ወደ ስልጣን አምጥታለች፤ ከስልጣናቸው ሽራለች፤ አስከፊ ጦርነቶችን አስተናግዳለች፤ ከእነዚህ ታሪካዊ ክስተቶች በተጨማሪ ግንቦት ያልተለመዱ ክስተቶች የተስተናገዱበት ወርም ነው። ታዲያ\nየ2011ን ግንቦት ልንቀበለው ሰዓታት ብቻ ቀርተውናልና ለዛሬ ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ካስተናገደቻቸው ታሪካዊ ክስተቶች መካከል ጥቂቶቹን ብቻ በአጭሩ ለመቃኘት እንሞክር። የመረጃው ምንጮች ልዩ ልዩ የታሪክ ጽሑፎች ናቸው። ግንቦት የልደት ወር ነው። ወታደራዊው የደርግ መንግሥት ከወደቀበት ጊዜ ጀምሮ እስከ 2004 ዓ.ም መገባደጃ ድረስ በመጀመሪያ በፕሬዚዳንትነት፣ በመቀጠልም በጠቅላይ ሚኒስትርነት ኢትዮጵያን የመሩት አቶ መለስ ዜናዊ የተወለዱት በግንቦት ወር ነው። የገናናው\nየሸዋ ንጉሥ የንጉሥ ሳህለሥላሴ የልጅ ልጅ፣ የታላቁ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምኒልክ የአክስት ልጅ እንዲሁም የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ አባት የሆኑት ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የተወለዱትም በግንቦት የመጀመሪያው ቀን በ1844 ዓ.ም ነበር። ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሐረርጌን ግዛት በማቅናትና በሚገባ በማስተዳደር ለንጉሥ ምኒልክ (በኋላ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ) ሀገር የማቅናት ተግባር ብርቱ አጋዥ የሆኑ ሰው ነበሩ። የውጫሌ ውል ያስከተለው የትርጉም ለውጥ መፍትሔው ጦርነት ሲሆንም ልዑል ራስ መኮንን ሠራዊታቸውን ይዘው ከአምባላጌ እስከ እስከ አድዋ በተደረጉት ውጊያዎች ላይ በመሳተፍ ጀግንነታቸውን አስመስክረዋል። በግንቦት\nወር መፈንቅለ መንግሥት የተሞከረባቸውና በግንቦት ወር አገር ጥለው የሸሹት የደርግ ሊቀመንበር ሌተናል ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምም የተወለዱት በግንቦት ወር ነው። ግንቦት የዕረፍት/ሞት ወርም ነው። በቀዶ ጥገና ህክምና ዘርፍ የመጀመሪያው ኢትየጵያዊ ሐኪም የሆኑት ፕሮፌሰር ዓስራት ወልደዬስ ያረፉት በግንቦት ወር 1991 ዓ.ም ነው። በታዋቂ የውጭ አገራት የሕክምና ሳይንስ ትምህርት ቤቶች የተማሩት ፕሮፌሰር ዓስራት ‹‹የጤና ጥበቃ ሚኒስትርነት ስልጣንን አልፈልግም፤ የተማርኩት ሐኪም ሆኜ አገሬን ላገለግል ነው›› በማለት ወገናቸውን አገልግለዋል። ከባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን የህክምና ማሰልጠኛ እንዲከፈት በተደጋጋሚ ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ ምክንያት የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሕክምና ትምህርት ቤትን እውን አደረጉ። የሕክምና ትምህርት ቤቱ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ዲን ሆኑ። የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሲቋቋምም የቴክኒክ ኮሚቴውን የመሩት እርሳቸው ነበሩ። ፕሮፌሰር ዶክተር ዓስራት በህክምናው ዘርፍም ‹‹አስራት የተባለ ጸበል ፈልቋል›› እስከመባል የደረሰ አንቱታን ያተረፉ ብቁ ሐኪም ነበሩ። ፕሮፌሰር\nዓስራት በመንግሥታት የሥራ ኃላፊዎች ይደርስባቸው የነበረውን ከፍተኛ ጫና ተቋቁመው ሐገራቸውን ሳይለቁ ህዝባቸውን ሲያገለግሉ የቆዩ አንጋፋ ባለሙያ ናቸው። ገናናውና መናኙ የታላቋ አክሱም ንጉሥ አፄ ካሌብ ያረፉት በግንቦት ወር በ20ኛው ቀን ነበር። አፄ ካሌብ ከአክሱምና አካባቢው አልፈው ቀይ ባሕርን ተሻግረው ከአይሁዳዊው ንጉሥ ፊንሐስ ጋር ያደረጉትን ጦርነት በድል አጠናቅቀው የደቡብ አረቢያ ሕዝቦችን ያስገበሩ ታላቅ ንጉሥ ነበሩ። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ስማቸው በጉልህ ከሚጠቀሱት እንስቶች መካከል አንዷ የሆኑት እቴጌ ምንትዋብ ያረፉትም በግንቦት ወር ነው። የአፄ\nበካፋ ባለቤት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ፣ ጎንደር የኢትዮጵያ ነገሥታት ማዕከል በነበረችበት ወቅት የነበራቸው ተፅዕኖ ከፍ ያለ እንደነበር ታሪክ ያሳያል። ባለቤታቸው አፄ በካፋ ከሞቱ በኋላ በተከታታይ በነገሡት በልጃቸው ዳግማዊ አፄ ኢያሱ እንዲሁም በአፄ ኢዮአስ ዘመነ መንግሥታት ትልቅ ሚና ነበራቸው። ከፖለቲካ ተሳትፏቸው በተጨማሪም ዛሬ ድረስ በበርካታ ጎብኚዎች የሚጎበኙ አብያተ ክርስቲያናትን አሳንፀዋል። ከዚሁ ከመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ታሪክ ሳንወጣ አፄ ሠይፈአርዕድ እና አፄ እስክንድር ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት በግንቦት ወር ነው። የንጉሠ\nነገሥት ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ባለቤት እቴጌ ጥሩወርቅ ውቤ ያረፉትም በግንቦት ወር 1860 ዓ.ም ነው። እቴጌዋ ያረፉትም ከባለቤታቸው ሞት በኋላ ከልጃቸው ከልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ ጋር ወደ እንግሊዝ ሲሄዱ ነው። አንጋፋውና ዝነኛው ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ ይቺን ዓለም በሞት የተለያት ግንቦት 29 ቀን 1984 ዓ.ም ነው። የጳውሎስ ኞኞ ስም ሲነሳ ወደአብዛኛው ሰው ዓዕምሮ የሚመጣው በቀለም ትምህርት ብዙም ሳይገፋ በድፍን ኢትዮጵያ ዝነኛና ተወዳጅ ለመሆን ያበቃው የጋዜጠኝነት ሥራው ነው። ጳውሎስ በተፈጥሮ የታደለው የማንበብ፣ የመጠየቅና የመመራመር ተሰጥኦ በጋዜጠኝነት ሙያው አንቱታን አትርፎለታል። በኢትዮጵያ\nድምፅ ጋዜጣ፣ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ፣ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እንዲሁም በኢትዮጵያ ራዲዮ ሲሠራ ‹‹ጋዜጠኝነትስ እንደጳውሎስ!›› የተባለለት ይህ ሰው፣ በርካታ መፅሐፍትንና ትያትሮችንም ለአንባቢያን አበርክቷል። ጳውሎስ የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር በተባ ብዕሩ ሞግቷል። ጳውሎስ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም፤ ብዙ የሙያ ዓይነቶችን ከባለሙያዎቹ ባላነሰ መልኩ ይከውን ነበር ይባላል። ባለውለታችንና\n‹‹የፊደል ገበታ አባት›› ቀኛዝማች ተሥፋ ገብረሥላሴ ግንቦት 26 ቀን 1992 ዓ.ም የዚህ ዓለም የመጨረሻ ቀናቸው ነበረች። ግንቦት የንግሥናና የሹመት ወር ነው። ዳግማዊ አጤ ምኒልክ ወራሻቸው የልጅ ልጃቸው ልጅ ኢያሱ ሚካኤል መሆኑን በአዋጅ ያሳወቁት ግንቦት በገባ በ10ኛው ቀን በ1901 ዓ.ም ነው። የልጅ ኢያሱ አባት ራስ ሚካኤል አሊ ደግሞ ‹‹ንጉሠ ወሎ ወትግራይ›› ተብለው የነገሡት በግንቦት ወር መገባደጃ ነው። የኢትዮጵያ\nሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ) አዲስ አበባን የተቆጣጠረውና ስልጣን የያዘውም በግንቦት ወር በ20ኛው ቀን በ1983 ዓ.ም ነው። ግንቦት የሽረት ወርም ነው። ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማርያም አገር ጥለው የሄዱትና ደርግ የወደቀውም በግንቦት ነው። ግንቦት ለብዙ የጎንደር ነገሥታት የስልጣናቸው ማብቂያ እንደነበርም በታሪክ ተመዝግቧል። ደም አፋሳሽ ጦርነቶች የታዩበት ግንቦት፣ የንጉሥ ምኒልክ (በኋላ ዳግማዊ አጤ ምኒልክ) እና የንጉሥ ተክለሃይማኖት ጦር እምባቦ ላይ በግንቦት የመጨረሻው ቀን ከባድ ውጊያ አደርጓል። የደጋማው ክርስቲያን ነገሥታት እና የግራኝ አሕመድ ጦርነቶች የከፉት በግንቦት ወር ነበር። የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር የደብረ ሊባኖስ ገዳምን ዘርፎ መነኮሳቱን በግፍ የጨፈጨፈውም በዚሁ በግንቦት ወር ነው። ግንቦት 25 ቀን 1788 ዓ.ም አመድ ከሰማይ መዝነቡም ግንቦት ያልተለመዱ ክስተቶች የተስተናገዱበት ወር ለመሆኑ ማሳያ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ኅብረት) እና የአንጋፋው ‹‹አዲስ ዘመን›› ጋዜጣ ምስረታ የተከናወነው በግንቦት ወር ነው። እሥራኤል ቤተ-እሥራኤላውያንን ከኢትዮጵያ ወደ እሥራኤል ለመውሰድ ‹‹ዘመቻ ሰለሞን (Operation\nSolomon)››ን ያካሄደችውም በዚሁ በግንቦት ወር ነው። በዘመቻ\nሰለሞን 14ሺ325 ቤተ-እሥራኤላውያን በ36 ሰዓታት ውስጥ፣ በ35 አውሮፕላኖች ከኢትዮጵያ ወደ እሥራኤል ተወስደዋል። ፎቶ ግራፍና ኢትዮጵያ/ኢትዮጵያውያንም የተዋወቁት ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አጤ ምኒልክ ግንቦት 13 ቀን 1875 ዓ.ም በተነሱት የመጀመሪያ ፎቷቸው ነው። በአጭሩ ግንቦት እና ኢትዮጵያ የቀን ምልኪያ አላቸው የሚያስብል ትስስር አላቸው።አዲስ ዘመን ሚያዚያ 30/2011በአንተነህ\nቸሬ", "passage_id": "d8eceb685edf554d5bd2f1f0fa35229d" }, { "passage": "በኢትዮጵያዊያን የዘመን አቆጣጠር የ2012 ዓመተምህረት የመጨረሻ ሳምንት ላይ እንገኛለን።ባሳለፍነው ዓመት ከተለያዩ የኪነጥበብ ዘርፎች የተውጣጡ እንግዶችን በመሰናዷችን ላይ አቅርበናል። ከግሩም ሀሳቦቻቸው ተቋድሰን ፣ የማይዘነጉ አፍታዎችን አሳልፈናል።ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ከመሸጋገራችን በፊት የአንዳንዶቹን ሀሳቦች እና ገጠመኞች ብናስታውሳችሁ ወደናል። መልካም ቆይታ። ", "passage_id": "b8b60a8605c5451479f1615fccc5a289" }, { "passage": "አገራችን አትዮጵያ በአለም ላይ ብቸኛዋ የአስራ ሦስት ወር ፀጋ ባለቤት አገር መሆንዋ ይታወቃል። እነዚህም ከመስከረም እስከ ጷግሜ ያሉት አስራ ሦስቱ ወራት ታዲያ የመጠሪያ ስማቸውን በየወራቱ ካለው የአየር ሁኔታና መሰል ጉዳዮች ጋር ተያይዞ የተሰጣቸው ሲሆን፤ ወራቱንም አስመልክቶ በጥንት ሊቃውንቶች ዘንድ የተነገሩ፤ እስካሁንም ድረስ በትውልዱ እየተነገሩ የዘለቁ የተለያዩ አባባል እና ስነ-ቃሎችም ይገኛሉ።እኛም በዛሬው የጥበብ እና ሕይወት መሰናዷችን አሁን የምንገኝበት የጥቅምት ወር እንደመሆኑ የወሩን የስያሜ መነሻ፣ ባህሪ እንዲሁም ከወሩ ጋር ተያይዘው ስለሚነገሩ ጥንታዊ አባባል እና ስነ-ቃሎች በጥቂቱም ቢሆን ዳሰሳ ልናደርግ ወደድን። መልካም ቆይታ\nየክረምቱ ወራት አልፎ በ አዲስ አመት ሲተካ ምድር በፀደይ ወር የልምላሜ ፀጋ ትፈካለች። በክረምቱ ወቅት የነበረው ዝናብና ጭጋጋማ አየርም በመስከረም ወር ቀስ በቀስ እየተወገደ ከጥቅምት ወር መባቻ አንስቶ መሉ ለመሉ መሬቱ ፍሬ ማፍራት ይጀምራል። ሜዳው፣ ሸንተረሩና መስኩ ሁሉ በለምለም ሳር እና በደማቅ አበቦች ተሸፍኖ ይታያል።የጥቅምት ወር ታዲያ የአበቦች መፍኪያ፤ ቡቃያዎች እሸት ማፍሪያ ወቅት በመሆኑ በተለይም በገበሬው ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ወር ነው። ንቦች በየአካባቢው የበቀሉ አበቦችን መቅሰም ጀምራሉ፣ ከብቶች የሚግጡት ሳር ለምለም ነውና ጠግበው ከወዲህ ወዲያ ይቦርቃሉ፣ ገበሬዎችም የቡቃያውን ማሸት የማሩን በቀፎ ውስጥ መሰራት እየተመለከቱ፤ ከሌሎቹ ወራት የበለጠ ጥቅምን እንደሚያገኙ በማሰብ ውስጣቸው በደስታ ይሞላል። ይህንንም ለማሳየት ይመስላል ወሩ ጥቅምት የሚል ስያሜን የተሰጠው። ጥቅምት የሚለው የወሩ መጠሪያ የግዕዝ ሥርወ ቃሉ ‹ጠቀመ› የሚል ሲሆን፤ ሠራ ወይንም ጠቃሚ ጊዜ የሚል ትርጓሜን ይይዛል።ወሩ በመስከረም ወር ያቆጠቆጡ አበቦች ሙሉ ለሙሉ የሚያብቡት፤ ንቦችም አበባውን ቀስመው ማርን መስራት የሚጀምሩበት ወር እንደመሆኑ ገበሬው ወደ ቀፎው የገባውን ማር ለመቁረጥ የሚዘጋጅበት ወቅት ነው። የጥቅምት ማር ደግሞ በመድሃኒትነቱ የሚመረጥ መሆኑን ብዙዎች ይናገሩለታል።‹ጥቅምት የማር እመቤት ናት፤ ያውም የማር እሸት› ይላሉ ካህሳይ ገ/እግዚአብሄር ህብረ ብዕር በተሰኘው መጽሐፋቸው ፤ በተለያዩ የአገራችን ገጠራማ አካባቢዎች ስላለው የማር አቆራረጥ ስርዓትም ሲያስረዱ፤ ‹‹በአገር ቤት ማር እንዲሁ በተገኘ ዕለት አይቆረጥም። ለምሳሌ፦ በጥቅምት ወር የሚቆረጠው ጥቅምት 17 ቀን በቅዱስ እስጢፋኖስ ዕለት ሲሆን በኀዳር ወር ደግሞ ኀዳር 12 ቀን በቅዱስ ሚካኤል ቀን ነው። ጥቅምት 17 ቀን የአበባ ወቅት የሚያበቃበት ቦታውን ለፍሬ የሚያስረክብበት ጊዜ ነው ተብሎም ይታመናል።›› በማለት በቀፎው ውስጥ የተሰበሰበውን ማር ለመቁረጥ አመቺውን ጊዜ ያስረዳሉ።በጥቅምት ወር በመላው የአገራችን ክፍሎች ወደሚገኙ ገጠራማ አካባቢዎች ለጉብኝትም ይሁን እግር ጥሎት በስራ ጉዳይ የሄደ ሰው በሚያየው ልምላሜ እና ተፈጥሯዊ ውበት እጅግ እረክቶና መንፈሱ ታድሶ እንደሚመለስም እሙን ነው።‹‹ጥቅምት ገበሬው የድካሙን የልፋቱን ዋጋ የሆነውን የምስራች የሚቀምስባት፣ ጥጆች የሚፋፉባት የአበባና የፍሬ ብቻ ሳይሆን የምርት ሲሳይ የሚታፈስባት ወርም ናት። ኧረ እንደ ጥቅምት የታደለ ማን አለ? ሌላው ቢቀር በጥቅምት ወር የተቆረጠ ዛፍ አይነቅዝም።›› በማለት ካህሳይ የጥቅምትን ወር የልምላሜ ትሩፋቶችን በመፅሃፋቸው ያስረዳሉ።ከዚህም በተጨማሪ በጥቅምት ወር የገበሬው ጎተራ ስለሚጎድል ቡቃያው ደርሶ እስኪሰበሰብ ድረስ ያለውን ይቆጥባል። ቡቃያው የደረሰ እና ወደ ጎተራ የገባ ጊዜ በቆሎውን፣ ስንዴውን፣ ማሽላውን ዘንጋዳውን እያማረጠ በደስታ በክረምቱ ወራት የተጎዳወን ሰውነቱን መጠገን ይጀምራል። ቢሆንም ‹‹ልጅን በጡት እህልን በጥቅምት›› እንዲሉ በጥቅምት ወር በቂ ምርትን የሰበሰበ ገበሬ ያገኘውን ምርት ሳያባክን በሥርዓቱ ቆጥቦ በመያዝ እስከ ሰኔና ሀምሌ መጠቀም ይኖርበታል። አለበዚያ መልሶ ለርሀብ እና ችግር መጋለጡ የማይቀር ነው።\nበአገራችን በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የመስከረምና የጥቅምት ወራት የአበባ ወራት (ዘመነ ጽጌ) በመባል ይታወቃሉ፡፡ ይህም ወቅት ሜዳና ሸንተረሩ በውብ አበቦች አሸብርቆና ለዓይን ግቡእ ሆኖ የሚታይበት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ መሠረትም ከመስከረም 26 እስከ ጥቅምት 6 ቀን ያለው ወቅት ‹ዘመነ ጽጌ፤ ወርኀ ጽጌ› ተብሎ ይጠራል፡፡ በግእዝ ቋንቋ ‹ጸገየ› ማለት ሲሆን ትርጓሜው ‹አበበ፤ አፈራ፤ በውበት ተንቆጠቆጠ፤ በደም ግባት አጌጠ፤ የፍሬ ምልክት አሣየ› እንደ ማለት መሆኑን ታደለ ገድሌ (ዶክተር) ‹ዘመነ ፅጌ› በሚል ርዕስ በፃፉት ፅሁፍ ላይ ይገልፃሉ።ዘመነ ጽጌ (ወርሓ ጽጌ) የሚከበረው ምድር በልምላሜና በውበት በምትንቆጠቆጥበት በዚህ ወቅት ነው፡፡ በየሳምንቱ እሑድ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ ማኅሌተ ጽጌ የሚቆሙትና ለሰዓታት ፀሎትን የሚያደርሱት ካህናት ቅድስት ድንግል ማርያምን በአበባ፣ በትርንጎ፣ በሮማን፣ በእንጆሪ እንዲሁም በሌሎች ለምለም እፅዋቶች እየመሰሉ ለፈጣሪ መዝሙርና ምስጋናን እንደሚያቀርቡም ታደለ በፅሁፋቸው ያስረዳሉ፡፡ለአርባ ቀናት ያህል የሚቆየው የዘመነ ጽጌ (ወርኃ ጽጌ) ወቅት መታሰቢያነቱ ለድንግል ማርያምና ለኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነም በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ይገለፃል። ቅድስት ድንግል ማሪያም ልጇን ይዛ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር በምድረ ግብጽ ሲሰደዱ የደረሰባቸውን እንግልት፣ መከራና ስቃይ ለማስታወስ፤ እንዲሁም ከግብፅ ምድር ወደ ናዝሬት የተመለሱበትን ወቅት ለመዘከር ሥነ-ስርአቱ ይከወናል። በዚህ ወቅትም ምእመኑ በተራ በተራ የጥቅምት ወር ካፈራቸው ልዩ ልዩ አዝርት እና አትክልቶች እየቆረጠ ምግብ በማብሰልና ጠላን በማዘጋጀት ማህሌት ቆመው ከሚያድሩ ካህናት እና ከቤተክርስትያኒቱ ምእመናት ጋር እየተገባበዘ ዘመነ ጽጌን ያሳልፋል።\nየጥቅምት ወር ከልምላሜ ፀጋው በተጨማሪ በማለዳው ውርጭ፣ በምሽቱ ቅዝቃዜና በለሊቱ ቁርም ጭምር በደንብ ይታወቃል። እንዲሁም ቀን ቀን የሚወጣው ጠራራ ፀሀይም ሌላኛው የጥቅምት ወር መገለጫ ነው።የዚህም የወቅቱ የአየር ሁኔታው ነፋሻማነትና መቀዝቀዝ ያለውን ጥቅም ካህሳይ በዚሁ ‹ህብረ ብእር› በተሰኘው መፅሃፋቸው ላይ ሲያስረዱ እንዲህ ይላሉ ‹በክረምት ወራት ውሃ ጠግቦ የባጀው መሬት ጠፈፍ እንዲል፣ ያሸተው አዝመራ ጎምርቶ፣ አፍርቶ በቶሎ እንዲደርስ (እንዲበስል) ነፋሱ አስፈላጊ ነው። የጥቅምቱ ነፋስ ታዲያ ብቻውን አይመጣም። ውርጭና ብርድን በአጃቢነት ይዞ ነው ከተፍ የሚለው።›› በማለት የወቅቱ ነፋሻማነት ለአዝመራው በቶሎ መድረስ ያለውን አሉታዊ ፋይዳ ያስረዳሉ።ታዲያ ለዚህም ነው የጥቅምት ወር በመጣና የቅዝቃዜው ነገር በታሰበ ቁጥር በብዙዎቻችን ዘንድ የሚታወቀው አንድ አባባል በህሊናችን ጓዳ ብቅ የሚለው። ‹‹በጥቅምት አንድ አጥንት››መቼም ይህ ሥነ-ቃል ጥቅምት ሲመጣ በብዙዎቻችን ዘንድ የሚነገር ሥነ-ቃል ነው። ታዲያ አጥንትን ለጥቅምት ወር ብቻ ማን ሰጠው በሌሎቹስ ወራት አጥንት አያስፈልግም ወይ የሚል ጥያቄ የሚያነሳ አይጠፋምና ለምን እንዲሀ እንደሚባል እንመልከት።ነገሩ እንዲህ ነው ቅድም ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርኩት የጥቅምት ወር ብርድ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው። ይሄንንም ብርድ ለመቋቋም ታዲያ ኃይልና ሙቀት ሰጪ ምግቦችን ሰውነታችን ማግኘት እንደሚገባው ይነገራል። ከእነዚህም ኃይልና ሙቀት ከሚሰጡ ምግቦች ውስጥ ደግሞ አንዱ ስጋ ነው። በመሆኑም የብርዱን ወቅት ተቋቋሞ ለማለፍ የስጋን አስፈላጊነት በማንሳት በጥቅምት አንድ አጥንት ይባላል። ታዲያ አጥንት ለመጋጥ አቅሙ የማፈቅድለትም በአጥሚት ሆነ በሌሎች ትኩስ እና ሰውነትን ሊያበረቱ በሚችሉ ምግቦች ወቅቱን እንዲያልፍ ይመከራል።ነገር ግን ይሄ ብቻ አይደለም። የጥቅምትን ወር ምክንያት በማድረግ የሚነገሩ አባባሎች ብዙ ናቸው። ‹ትምህርት በልጅነት፤ አበባ በጥቅምት ያምራል›፣ ‹ልጅን በጡት፤ እህልን በጥቅምት›፣ ‹አትትረፊ ያላት ወፍ፤ በጥቅምት ትሞታለች›፣ ‹ውሃ የጥቅምት ነበርሽ ማን በጠጣሽ፤ ምክር የደኻ ነበርሽ ማን በሰማሽ›፣ ‹ያልታደለች ወፍ በጥቅምት አይኗ ይጠፋል› እኚህና ሌሎች እኚህን የመሳሰሉ ተረት እና አባባሎች በጥቅምት ወር ተዘውትረው ሲነገሩ ይሰማል።ከዚህም በተጨማሪ ስለ ጥቅምት ወር ልምላሜ በግጥሞች፣ በመፅሀፍቶች፣ በሙዚቃዎች ብዙ የተባለ ሲሆን ለዚህም ‹‹የጥቅምት አበባ›› በሚለው የንዋይ ደበበ ዘፈን እንደ አንድ ማሳያ ያገለግለናልና እስኪ ግጥሙን በጥቂቱ ወደ እናንተ ላድርስ የዜማውን ነገር ለእናንተው ትቼዋለው።የጥቅምት አበባ፤ የጥቅምት አበባ፤\nየጥቅምት አበባ ነሽ አሉ፤\nአወድሽው አካሌን በሙሉ።\nየጥቅምት አበባ፤ የጥቅምት አበባ፤\nየጥቅምት አበባ ለሽታ፤\nለኔ ግን ጣልሽብኝ ትዝታ።\nንብ ሆኜ መጥቼ እንዳይሽ፤\nፈገግ ብሎ ይቆየኝ ጥርስሽ፤\nእመጣለሁ ጠብቂኝ በርሬ፤\nታዲያ ላልመለስ አፍሬ፤\nተጣልቷል አይኗ ከአይኔ ጋር፤\nአስታርቁኝ እንዴት ይነጋል፤\nንገሯት አለሁ ትበለኝ፤\nበእሷ ነው እረፍት የማገኝ……እያለ የጥቅምት አበባን ውበት፣ የንቦቹን ወቅቱን ጠብቆ ማር መስራት በአጠቃላይ የወቅቱን ልምላሜና ድምቀት በልዩ ሁኔታ በዜማ ይገልፀዋል።\nኮሮና፣ የጎርፍ አደጋ፣ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንዲሁም የአንበጣ መንጋ ስጋት እና የዘንድሮው የጥቅምት ወር\nየዘንድሮው ጥቅምት እንደወትሮዎቹ የጥቅምት ወራት ሁሉ ልምላሜን የታደለና ለገበሬውም መልካም ተስፋን በመያዝ የደረሰ አይመስልም። በኮሮና ወረርሺኝ ሳቢያ እንቅስቃሴዎች በመገደባቸውን ምርታማነት መቀነሱ ይነገራል። በተጨማሪም በተለያዩ የአገሪትዋ ክፍሎች ተከስቶ የነበረው የጎርፍ አደጋ የገበሬውን ማሳ በእጅጉን ያበላሸ፣ አርሶ አደሩን ከቤት ንብረቱ ያፈናቀለ፣ ከብቶቹን ያጠፋና ጎተራውንም ያራቆተ ነበር። በተጨማሪም በየአካባቢው በሚከሰቱ ኹከት እና ብጥብጦች ሳቢያ የብዙሃን ህይወት ጠፍቷል፣ ቤት ንብረት ተቃጥሏል እንዲሁም የደረሰ ማሳ ወድሟል።ከዚህ ሁሉ በላይ ግን በአሁኑ ሰአት በአገራችን በስፋት እየተሰራጨ የሚገኘው የአንበጣ መንጋ የገበሬውን ማሳ ያበላሸና በከፍተኛ ደረጃ ምርታማነቱን እያሳጣው የሚገኝ ጉዳይ ሆኗል። ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሳምንት እንደተናገሩት ከሆነ የአንበጣ መንጋው በአሁኑ ሰዓት በአጠቃላ በ240 ወረዳዎች ላይ የተከሰተ ሲሆን በእነዚህም ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ 750 ቀበሌዎች ላይ መንጋው በሰብል ላይ ጉዳት አድርሷል።በእነዚህም አካባቢዎች በድምሩ 4 ሚሊዮን ሔክታር ታርሶ እንደነበር የጠቆሙት ጠ/ሚኒስቴሩ ከዚህም ውስጥ 420 ሺህ ሔክታር የሚሆን ሰብል ውድመት እንደደረሰበት አስታውቀዋል።ታዲያ ይህ ሁሉ እየሆነ ባለበት ወቅት ስለ ጥቅምት አበባ፣ ስለ ልምላሜ እና ስለ አጥንት ማውራቱ ተገቢ ባይሆንም፤ እኛ ግን ለአገራችን መልካሙን ሁሉ እየተመኘን የወቅቱን ቀደምት ታሪክና የአየር ሁኔታ ለማስታወስ ያህል ይሄን አለን። ፈጣሪ በአገራችን ላይ አጥንት የሚሰብረውን አጥፍቶ የሚጠግነውን ያብዛልን። ሰላምቅጽ 2 ቁጥር 103 ጥቅምት 14 2013", "passage_id": "75b6c57b7bb7eb30315bf0ba3e4be368" }, { "passage": "ዘመን ዘመንን እያስረጀ ደግሞም እያደሰ የ2011 የመጨረሻው ሳምንት ላይ ተገኝተናል። ትርጉም ያልተበየነለትና ረቂቅ የሆነው ጊዜ እንዲህ በዘመን ተከፍሎ 365 ቀናትን ሲሻገር እንደ አዲስ በምዕራፍ ይከፈታል። አሮጌ ሲሸኝ አዲስ ይተካል፤ የቀደመው ቢያልፍም ለነገ መሠረት ስለሚሆን በታሪክነት ግን ይመዘገባል።\n2011 በኢትዮጵያ እጅግ ብዙና የተለያዩ ዜናዎች የተሰሙበት ዓመት ነበር። በተለይም ፖለቲካው ሳይተኛ የከረመበት ነው ማለት ይቻላል። በፖለቲካ ሰበብ እንደ አገር ሕዝቡ፣ እንደ ሙያ ደግሞ በርካታ ዘርፎች ተፈትነዋል። ከዚህም መካከል የጥበቡ ዘርፍ አንዱ ሳይሆን አልቀረም። በተለያየ የጥበብ መስክ ላይ የተሰማሩ የጥበብ ባለሙያዎችም በዓመቱ ያለፈውን የጥበብ ነገር ሲያነሱ የአገርን ነባራዊ ሁኔታና ክስተቶችን መጠቃቀሳቸው አልቀረም። ፖለቲካው ማንም ሊያመልጠው የማይችለው ነዋ!አዲስ ማለዳ በዓመቱ በኢትዮጵያ በዋናነት የሚጠቀሱ የጥበብ ዘርፎች ያለፉትን ክዋኔዎች፣ የተገኙትን አዳዲስ ነገሮችና የሚሻገሩ ፈተናዎችም ይሁን ስኬቶችን ልትመዘግብ ወደደች።ሙዚቃበ2011 እጅግ በርካታ ነጠላ ዜማዎችና በድምሩ 15 የሚጠጉ አልበሞች ለአድማጭ ቀርበዋል። ከነ “ምን ላድርግልህ?” ውዝግብ ጀምሮ ነጠላ ዜማዎችን በሚመለከት ፌዝና ቀልድ መሰል ሥራዎች ሙዚቃ ተብለው ተሠርተዋል። አንዳንዴም “ወዴት እየሔድን ነው?” የሚል ጥያቄ የሚያስነሱና የያዙት ጭብጥ ኢትዮጵያዊ ሥነ ምግባር የጎደለው “ዘፈኖች” ተሰምተዋል።በአንጻሩ በዳዊት ጽጌ “አማን አማን” የተሰኘ ሙዚቃ የከፈተው 2011፣ አዳዲስ አቀራረብ፣ ዕይታና ጭብጥ የያዙና አተያይን የቀየሩ እንደ አብርሃም በላይነህ “እቴ አባይ” ዓይነት በጣት ሊቆጠሩ ከሚችሉ የሙዚቃ ሥራዎች በርካታ ተመልካችን ማግኘት እስከቻለው የዘቢባ ግርማ “ገራገር” ድረስ ብዙ ያሳየ ነው።\nየሙዚቃ ባለሙያዎች ከነጠላ የዜማ ሥራዎች ይልቅ በአልበሞች ላይ አስተያየት መስጠት መርጠዋል። እርግጥም ነው ለነጠላ ዜማዎቹ መካሻ የመሰሉ በጠራራ ፀሐይ መካከል ጥላ እንደሚሆን ደመና ደርሰው ያረጋጉ አልበሞችም ተሰምተዋል። ግጥምና ዜማ ደራሲ እንዲሁም የሙዚቃ አቀናባሪ አማኑኤል ይልማ በበኩሉ በ2011 የነበረውን የሙዚቃ ሁኔታ ከአገር ሰላምና መረጋጋት ጋር አስተሳስሮታል።“አገር ሲረጋጋ ነው ሙዚቃ መስማትም ሆነ መጨፈር የሚቻለው፤ ይህ መረጋጋት በብዙ የአገራችን አካባቢዎች ባለመሆኑ ግን በ2011 ብዙ አልበሞች የወጡ ቢሆንም አልተሰሙም” ብሏል። በሰላም ማጣት ምክንያት የተሰረዙ ኮንሰርቶችን፣ የአስቴር አወቀን የአልበም ሥራ ጨምሮ ተራዝመው የቆዩ ሥራዎች መኖራቸውንም ያስታውሳል። ይህም ሁሉ ሲደማመር 2011 ለሙዚቃው ጥሩ ዓመት ነበር ለማለት እንደማያስደፍረው አማኑኤል ለአዲስ ማለዳ ገልጿል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ትንሳኤ ነው የተባለለት “አውታር” የተሰኘው የሙዚቃ መገበያያ መተግበሪያ የተዋወቀውና ወደ አገልግሎት የገባው በ2011 ነው። ይህም ሕገወጥ ቅጂን ለመቆጣጠር ይረዳል የተባለለት ነው። ከ50 ዓመታት በፊት የተሠሩ የኢትዮጵያ ሙዚቃዎችን የቅጂ መብት የሚጠብቅ መሆኑንም ከዚህ ቀደም አዲስ ማለዳ ማስነበቧ ይታወሳል።ቴአትርአዲስ አበባ ላይ ብቻ “ተበራክተው” የሚገኙት ቴአትር ቤቶቻችን፣ በርካታ ተብሎ በቁጥር ሊጠቀስ በማያስደፍር መልኩ ልንሸኘው በዝግጅት ላይ ባለው 2011 አዳዲስና ነባር ተውኔቶች ተዘጋጅተው አቅርበዋል። አዲስ አበባ ቴአትርና ባሕል አዳራሽ መቅረብ ከጀመረው “አሉላ አባ ነጋ” ታሪካዊ ቴአትር አንስቶ ለኹለተኛ ጊዜ በብሔራዊ ቴአትር መድረክ የወጣው “ባቢሎን በሳሎን”፤ ከአዲስ አበባ ውጪ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች እየተንቀሳቀሰ ለዕይታ እስከቀረበው የአገር ፍቅር ቴአትር የተመደረከው “ከመጋረጃው ጀርባ” ድረስ ለተመልካች ቀርበዋል።በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የቴአትር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ደስታ አስረስ፤ 2011 ለቴአትር ወርቃማው ዓመት ነበር ብለዋል። ለዚህም ምክንያታቸው ታግደው የነበሩ ቴአትሮች ለዕይታ ፈቃድ ማግኘታቸው ነው። ለዚህም በቴአትር ቤቱ አሁን በዕይታ ላይ ያለው የተክሌ ደስታ “መንታ መንገድ” ቴአትር ተጠቃሽ ነው።“ይህ ጥበብ በነጻነት መሠራት መጀመሩን ማብሰሪያ ነው” ያሉት ደስታ፤ በታገዱ ቴአትሮች ምክንያት 2010 ከ2011 አንጻር ድብታ የነበረበት መሆኑን አስታውሰዋል። ከዛም ባሻገር ከበርካታ ዓመታት በኋላ ወደ አገራቸው የተመለሱ የቴአትር ቤቱ የቀድሞ ባለሙያዎች ጋር የተደረጉ ምክክሮችና የሐሳብ ልውውጦች ጠቃሚ እንደነበሩም ጠቅሰዋል።ከዚህም ሁሉ በኋላ ሃያስያን ሊመሰክሩላቸው የሚችሉ የቴአትር ሥራዎች መውጣታቸውን አያይዘው አንስተዋል። በቴአትር ቤቱ ደረጃውን የጠበቀና ለቴአትር ሥራ የተመቸ ግንባታ ሥራ መጀመሩም በ2011 የተመዘገበ ነው። ዓመቱ በብሔራዊ ቴአትር የተመልካች ቁጥር የጨመረበትና ጥበባዊ ፋይዳቸው ከፍተኛ የሆኑ ቴአትሮች የቀረቡበት እንደነበር በፍቃዱ ከፈለኝ፤ የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊው ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል። በተለይም “ባዶ እግር” የተሰኘው ቴአትር ግሪክ ድረስ ሔዶ ለዕይታ መቅረቡም በዓመቱ ከተከናወኑ አበይት ኩነቶች መካከል ይጠቀሳል።አገር ፍቅር ቴአትር ሌላው በስስት የሚታይ አንጋፋ ቴአትር ቤት ነው። በተመሳሳይ ራስ ቴአትርንም ማንሳት ይቻላል። ቴአትር ቤቶች ለቴአትሩ ዕድገት ያላቸው አስተዋጽዖ ከፍተኛ እንደመሆኑ፤ ለቴአትር ቤቶች የሚሰጠው ትኩረት መጠንም ቀላል ግምት የሚሰጠው አይሆንም። በዚህ መሰረት 2011 ራስ ቴአትር ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲገነባ ለግንባታ የሚሆን ቦታ ያገኘበት፣ አገር ፍቅር ቴአትርም ይዞታውን በማሻሻል ታሪካዊ ቅርጹን ሳይለቅቅ እድሳትና መስፋፊያ እንዲያገኝ ከከተማ አስተዳደሩ ትኩረት እንዲሁም ፈቃድ ያገኙበት ዓመት ነው።ብሔራዊ ቴአትር “አልቃሽና ዘፋኝ” ከበርካታ ዓመታት በኋላ እንዲሁም “ባቢሎነ በሳሎን” ዳግም ለዕይታ ቀርበዋል። “አንድ ለአንድ”፣ “ምስጢሩ” እና “እምዬ ብረቷ” በዓመቱ የታዩ አዳዲስ ቴአትሮች ሲሆኑ፤ “ባዶ እግር” 2011ን ከቀደመው ዓመት ተሸጋግሯል። በአገር ፍቅር ቴአትር “ነቃሽ”፣ “ሰፈረ ጎድጓዳ” እና “የመንግሥት ሥራ” አዲስ የገቡ ቴአትሮች ሲሆኑ ተሻግረው 2011 ላይ የታዩት ቴአትሮች “የጉድ ቀን”፣ “ገራገሩ” እና “ከመጋረጃው ጀርባ” ናቸው።ስዕልየሥዕል ጥበብ በቅርበት ከሚያውቁት ውጪ ብዙ ትኩረት የሚሰጠው ዘርፍ ባይመስልም ብዙዎች ግን ባዩበት አጋጣሚ ማድነቃቸው አይቀርም። ከስዕል ጥበብ ባሻገር በጥቅሉ የዕይታዊ ጥበባት ነገር የሚያስጨንቃቸው ጥቂት አይደሉም። ከዚህ አንጻር በተለይም በአዲስ አበባ ሊከናወኑ ዕቅድ የተያዘላቸው ከተማዋን የማስዋብ ሥራዎች ለዕይታ ጥበብ ምላሽ ሊሰጡ እንደሚችሉ ይገመታል። ይህን ተከትሎ በመስታወት የታጠሩ የሚመስሉ ሕንጻዎች ግንባታ ተገትቶ በዲዛይን ሥራ ጥበብና ኢትዮጵያዊነት የታከለበት ሥራ የሚጠበቅ ይሆናል።እስከዛው ወደ ስዕል ጥበብ ብቻ ስናተኩር፤ ምንም እንኳን የተሠራ ዳሰሳ ባይኖርም ስዕል ከሌሎች የጥበብ ውጤቶች በተሻለ ብዙ ዓውደ ርዕዮች የሚስተናገዱበት መስክ ይመስላል። በመደበኛነት መስቀል አደባባይ በሚገኘው አዲስ አበባ ሙዝየም፣ ብሔራዊ ሙዝየም፣ ጀርመን የባሕል ማዕከል፣ ጉራማይሌ አርት ጋለሪ፣ ፈንድቃ የባሕል ማዕከል፣ ብሔራዊ ቴአትር፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚና ሌሎችም ማዕከላት ከሚገኙት ባሻገር በተለያየ ጊዜ አዳዲስ የስዕል ዓውደ ርዕዮች ለዕይታ ቀርበዋል።\n“ሰዓሊ እንደ ዜጋ የማኅበረሰቡ አካል ነውና አገራዊ ጫናን ይካፈላል” ያለው እያዩ ገነት፣ ሰዓሊና መምህር ነው። በዚህም ምክንያት በቋሚነት የስዕል ዓውደ ርዕይ ከሚያቀርብባትና ከሚያስተምርባት ባሕር ዳር ከተማ ጨምሮ በአገር ውስጥ የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ ክስተቶች በዚህ የጥበብ መስክ ላይ ተጽዕኖ መፍጠራቸውን ይገልጻል። ይህም በግሉ ማለትም በስዕል ማሳያው ከገጠመው የተመልካች ቁጥር መቀነስ ጀምሮ በሰዓልያን ላይ የተፈጠረው አገራዊ ምስል ድረስ የሚዘልቅ ነው ብሏል።“ጥበብ በባሕሪው መነካትን ይጠይቃል” የሚለው እያዩ፤ እየታዩ ያሉ ኩነቶች መካከል ለሰዓሊው ግብዓት የሚሆኑ እንዳሉ ይጠቅሳል። በዓመቱ በተፈጠሩ አገራዊ ቀውሶች ምክንያት “ፍቅር ያሸንፋል” የሚሉ እንዲሁም ዛሬን መሻገርና ነገን በተስፋ መጠበቅን የሚያመላክቱ የስዕል ሥራዎች እንደተሠሩም አያይዞ ያነሳል።\nበመጠን ከሚያይለው መጥፎ ነገር ትንሽ በሆነ ጥሩ ነገር ላይ ማተኮርን እመርጣለሁ የሚለው እያዩ፤ በ2011 የሆኑ ክስተቶች ሁሉ ራሱን ጨምሮ አርቲስቱ እንደ አስታራቂ ዳኛ እንዲሆን አድርጓል ባይ ነው። በተለይም “ኢትዮጵያ” የሚለው ሥም ከዓመታት በኋላ ደጋግሞ መጠራት መጀመሩ በሰዓሊ ልብ ውስጥ እንዲሁም ሸራ ላይ ቀለም ጨምሯል ሲል ለአዲስ ማለዳ አስተያየቱን አካፍሏል።ከዚሁ ጋር በተያያዘ “ነጻ ጥበብን ፍለጋ – ማንነት” የተሰኘ ዓውደ ጥናት በ2011 ከቀረቡ ስዕል ተኮር መድረኮቸ መካከል ተጠቃሽ ነው። በዚህ ዓውደ ጥናት ላይ ከአለ የስዕል ትምህርት ቤት፣ ከሰዓሊያን ማኅበር እንዲሁም ከኦሮምያ የሰዓልያን ማኅበር የተውጣጡ ባለሙያዎችና ሌሎችም የተሳተፉበት መድረክ ነው። በዚህም ዓውደ ጥናት ላይ አገር በቀል የአሳሳል ጥበብን ይዞ ስለመገኘት፣ ስለቅጂ ሥራዎች አግባብ አለመሆን፣ ሰዓሊ የራሱን አሻራና ፈጠራ የሚያክልበት ሥራዎችን ከማበርከት አንጻር ባለሙያዎችና የኪነ ጥበብ ሰዎች ተወያይተዋል።ፊልምከቅርብ ዓመታት ወዲህ የፊልም ገበያው እየተቀዛቀዘ እንደሆነ ቢነገርም በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያን የፊልም ኢንዱስትሪ ከአውሮፓ የፊልም ተጽዕኖ ይልቁንም ይስተዋል ከነበረው የታሪክ ጭብጥ መመሳሰል ነጻ በማድረግ ረገድ ጠንካራ ሥራዎች ተሠርተዋል። “ቁራኛዬ” እንዲሁም “ሦስተኛው ዓይን” ዓይነት ፊልሞች ለዚህ ተጠቃሽ ምሳሌ ሆነው መቅረብ ይችላሉ። በተመሳሳይ በተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ረገድም የነበሩት የዘለቁበት አዳዲስ ተከታታይ የቴሌቭዥን ፊልሞችና ድራማዎችም ለዕይታ የቀረቡበት ዓመት ነው፤ 2011።ከአላቲኖስ የፊልም ሠሪዎች ማኅበር ምኒልክ መርዕድ፤ በዓመቱ ጥሩ ፊልሞች ለዕይታ መቅረባቸውን ጠቅሷል። ከታሪክ፣ ከገጻ ባሕሪ ግንባታ፣ ከካሜራ ቴክኒክና መሰል የፊልም ሥራ ከሚፈልጋቸው ሥራዎች አንጻር የተሻሉ የሚባሉ ፊልሞች ተሠርተዋል ብሏል። ከጭብጥ አኳያም ቀድሞ የነበረው የሮማንቲክ ኮሜዲ ዘውግ በ2011 ብዙ እንዳልታየና ይልቁንም አገራዊና ፖለቲካዊ ምልከታ እንደነበራቸው አንስቷል። በአንጻሩ የፊልም መሰረቆች በዓመቱ ለፊልሙ ዘርፍ መጥፎ ጎን ሆኖ እንዳለፈ ያወሳው ምኒልክ፤ “ፊልሞች ሲኒማ ቤት ታይተው ሠሪዎቹ ዲቪዲ ወይም ሌላ መንገድ ተከትለው ፊልሙን ለማከፋፈል ሳያስቡ ሲሰረቁ ነበር” ሲል ለአዲስ ማለዳ አስታውሷል።ይህን በተመለከተ በቅርቡ ከሲኒማ ቤት በሞባይል ቅጂ ተሰርቆ የወጣው “ሦስተኛው ዓይን” ፊልምን የሰረቀው ሰው ለፍርድ መቅረቡን እንደማሳያ ያነሳችው የፊልም ፕሮድዮሰሮች ማኅበር ፕሬዝዳንት አርሴማ ወርቁ ናት። ለማኅበሩ አቤቱታ ይዘው ከቀረቡ ኹለት የተሰረቁ ፊልሞች መካከል ነበር፤ “ሦስተኛው ዓይን”።እንደ አርሴማ ገለጻ፣ ዓመቱ የተመልካች ቁጥር የጨመረበት ነው። በፊልም ዘርፉ በዓመቱ በፊልም ማሳያ ቤቶች ማሰራጫ መንገዶችና ከማዘመን ጀምሮ ፊልሞች ሲሰረቁ ከምንጩ መያዝ የሚችልበት አሠራር መፈጠሩም በ2011 የተመዘገበ ስኬት መሆኑን ጠቅሳለች። መገናኛ ብዙኀን የቀደመውን ትችት ትተው፤ አዳዲስ ዘውግና ሐሳብ በያዙ ፊልሞች ምክንያት ለዘርፉ የሰጡት ትኩረትም የላቀ ሚና አለው ብላለች።መጻሕፍት“አንባቢ ጠፋ፤ የለም” በሚባልበትና ስለንባብ በሚሰበክበት ጊዜ የመጻሕፍት ነገርም ከዚህ የራቀ አይደለም። ሞቅ ያለውን የፖለቲካ እንቅስቃሴ ተከትለው የሚወጡ የመጻሕፍት ሥራዎች ብዙውን ጊዜ እንደጋዜጣ ወቅታዊ ጉዳይን የያዙ፤ እንደማኅበራዊ ገጽ የግለሰቦችን ግላዊ ዕይታ ብቻ ያቀፉ በመሆናቸው ለታሪክ ግብዓት ወይም ለእውቀት ተጨማሪ ፋይዳ ሳይሰጡ ለገበያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ሲቀሩ ታዝበናል።የእነሆ መጻሕፍት ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ ኤርምያስ በላይነህ፤ እንደውም በአገሪቱ የፖለቲካ ምኅዳር ሰፋ እንደመባሉና በርካቶችም ከውጪ እንደመምጣታቸው ፖለቲካ ቀመስ ሥራዎች በበቂ ሁኔታ ተሠርተዋል ማለት እንደማይቻል ይጠቅሳል። በአንጻሩ በ2010 ከፖለቲካው ጋር ተያይዞ ይወጡ የነበሩ መጻሕፍት የተሻለ ተነባቢ እንደነበሩ ነው የጠቀሰው። ከዛ በኋላ ግን የትርጉም፣ የልብወለድ፣ ፍልስፍና እና ሥነ ልቦና ባሻገር ሲልም የታሪክ መጻሕፍት የአንባቢን ትኩረት ስበዋል ይላል። በድምሩ ግን የመጻሕፍ ገበያው ጥሩ አልነበረም፤ እንደ ኤርምያስ ገለጻ።የታሪክ ባለሙያ እና የቋንቋ መምህር እንዲሁም በሚዩዚክ ሜይዴይ የመጻሕፍት ውይይት መድረክ ላይ በአወያይነት የሚታወቀው ሰለሞን ተሰማ ጂ. ከ2010 በተሻለ ጠቃሚ ሐሳቦች በመጻሕፍት የተነሱበት ዓመት ነው ይላል። ይልቁን ከኅትመትና ስርጭት ጋር በተያያዘ የመጻሕፍት ዋጋ በእጥፍ መጨመሩ፣ በሰላምና መረጋጋት እጦት ምክንያት ስርጭት ላይ መስተጓጎል መፈጠሩን እንደችግር ያነሳል።በዓመቱ ትኩረት ያገኙ መጻሕፍትም መኖራቸው አልቀረም። አንዳርጋቸው ጽጌ በእስር ቆይታቸው ያዘጋጁት ‹‹ትውልድ አይደናገር፤ እኛም እንናገር›› በዚህ የሚጠቀስ ነው። አልፎም የቀረ የመሰለን አሳታሚ የማይጠቀስበት የመጽሐፍ ሕትመትም በተስፋዬ ገብረአብ ‹‹የቲራቮሎ ዋሻ›› ተመልሷል። የሙሉጌታ አረጋዊ ታሪክ ቀመስ ልብወለድ ‹‹አብራክ›› ለውይይት የቀረበ፤ በጄኔራል መርዕድ ንጉሤ ሕይወት ዙሪያ የተዘጋጀው ‹‹ለአገር ክብር ለወገን ፍቅር›› መጽሐፍም ያነጋገረ ነበር። አዲስ ማለዳ ባላት መረጃ ሕይወት እምሻው እና ዓለማየሁ ገላጋይ ባልተለመደ ሁኔታ እያንዳንዳቸው ሁለት መጻሕፍትን ለአንባብያን ያበረከቱት በዚሁ ዓመት ነው።", "passage_id": "dbfacdc28f9d472bc7a657edcc00dcb6" }, { "passage": "ነገር ግን ሌሊት 10 ገደማ የሆነውን ማንም አልጠበቀውም። ሃገር ሰላም ብለው እንቅልፍ ላይ ያሉ አዲስ አበባውያንን ቀልብ የገፈፈ ክስተት። ከ100 በላይ ሰዎችን የቀጠፈ ጉድ።\n\nኒው ዮርክ ታይምስ ጋዜጣ በዕለቱ ያወጣው ዕትም ላይ የአዲስ አበባ ሕዝብ ቁጥር በግምት 3 ሚሊዮን ይሆናል ይላል። ታድያ ይህን ሁሉ ሰው በአንዴ 'ክው' የሚያደርግ ምን ሊሆን ይችላል?\n\nየተሰማው ፍንዳታ ነበር። ከበ...ድ ያለ ፍንዳታ። ከጎተራ እስከ ሰሜን ሆቴል የተሰማ። ከአቃቂ እስከ ኮተቤ ቀልብን የገፈፈ።\n\nመታሰቢያ ሸዋዬ ይልማ የዛኔ የ12 ዓመት ታዳጊ ነበርኩ ትላለች፤ የ7ኛ ክፍል ተማሪ። ቢሆንም ክስተቱን መቼም አትረሣውም። \n\n«የዛን ሰሞን ከሁለት ሳምንት ጀምሮ ትምህርት ተዘግቶ ነበር። ልክ ጓድ መንግሥቱ ኃይላማርያም ከሃገር ኮበለሉ ተብሎ የተነገረ 'ለት [ግንቦት 13] ቤተሰቦቻችን ለቅመውን ወደ ቤት ገባን። ከዚያ በኋላ ትምህርት አልነበረም። አስጨናቂ ሳምንት ነበር። ልክ በሳምንቱ [ግንቦት 20] የኢህአዴግ ሠራዊት አዲስ አበባ ገባ። ከዚያ በኋላ የጥይት ድምፅ አልነበረም፤ ትንሽ ጋብ ብሎ ነበር።»\n\n• የዛሬ 30 ዓመት... የኮ/ል መንግሥቱ አውሮፕላን ለምን አልጋየም?\n\nአዲስ አበባ ከዚያ በፊት በነበሩት ሳምንታት የጥይት ይሁን መሰል ፍንዳታዎች ድምፅ ይህን ያህል ብርቋ አልነበረም። መታሰቢያ ትቀጥላለች. . .\n\n«ከእንቅልፋችን የቀሰቀሰን ፍንዳታው ነበር። መሬት 'ሚያንቀጠቅጥ ዓይነት ፍንዳታ ነበር። በዚያ ላይ ጨለማ ነው። ምን እንደሆነ አላወቅንም፤ እስከዛን 'ለት ከሰማናቸው ፍንዳታዎችም በጣም የተለየ ነበር። ሁሉም ሰው ተነሳ፤ ነገር ግን ግራ በገባው ስሜት ውስጥ ነበር። ጦርነት ነው እንዳንል ጦርነቱ አልቋል. . .ምን እንበለው? አየቆየ ሲመጣ የጥይት የሚመስሉ ትንንሽ ፍንዳታዎች መስማት ጀመርን።»\n\nፍንዳታውን የሸሹ ሰዎች እግራቸው ወደመራቸው መትመም ያዙ። ወደ እነመታሰቢያ ሠፈርም የመጡ አልጠፉም።\n\n«እንግዲህ አስበው ሠፈራችን ሰሜና ማዘጋጃ ነው። ግን ፍንዳታውን የሸሹ ሰዎች በግምት ከፍንዳታው አንድ ሁለት ሰዓት በኋላ እኛ ሠፈር ደርሰዋል። ወላጆቼ ወጥተው ሲጠይቁ ፍንዳታ እንደሆነ ተረዱ። የሚቀጣጠል ነገር እንዳለም ከሰዎቹ ሰሙ። ወላጆቼም ግራ ገብቷቸው ነበር። እኛም እንውጣ ወይስ ትንሽ እንጠብቅ ዓይነት ነገር ነበር የነበረው። መጨረሻ ላይ አንድ ድብል...ቅ ያለ ፍንዳታ ተሰማ። በጣም ከባድ ከመሆኑ የተነሳ መስኮታችን ሁላ የሚረግፍ ነበር የመሰለው። ከዚያ በኋላ ነው ፍንዳታውም የተረጋጋው፤ ቀኑም እየነጋ መጣ።»\n\nየጦር መሣሪያ ማከማቻ\n\nይድነቅ አብርሃ ክስተቱን ለመዘገብ ካሜራቸውን አንግበው ወደሥፍራው ካመሩ ሰዎች መካከል ነበር። ይድነቅ በወቅቱ የሚያነሳቸውን ፎቶዎችን እና ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለሕወሓት ማሕደር ክፍል ያስረክባል። ቢሯቸው የነበረው ደግሞ አቡነ ጴጥሮስ አካባቢ የነበረው የኢትዮጵያ ራድዮ ዋና መሥሪያ ቤት። \n\n«ፍንዳታውን ስንሰማ የኛ 'ክሩ' ቪዲዮ እና ፎቶግራፍ ለማንሳት ወደዚያ ሄደ። የፈነዳው የጦር መሣሪያ ማከማቻ የነበረ ሥፍራ ነበር፤ በርካታ ብረታብረቶችም ነበሩ ሥፍራው ላይ። ፍንዳታው አካባቢው በጭስ እንዲዋጥ አድርጎ ነበር። ብዙ ተጎጅዎችም ነበሩ። በርካቶች ሞተዋል፤ የቆሰሉም የትየለሌ ነበሩ። እኛ ፎቶ እና ቪደዮ ስናነሳ የነበረው እዚያ የነበረውን ሁኔታ ነበር።» \n\nያኔ ጎተራ፤ እንደዛሬ በማሳለጫ ሳትከበብ ግዙፍ የነዳጅ ማከማቻ እና የለስላሳ ፋብሪካ አልተለይዋትም ነበር። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት መናኸሪያም ነበረች ጎተራ። «በጣም አስገራሚው ነገር እንዲያውም ነዳጅ ማደያው አለመፈንዳቱ ነው» ትላለች መታሰቢያ።\n\n«ጎተራ፤ አሁን ያለውን ቅርፅ ሳይዝ በፊት 'ኮንፊውዥን... ", "passage_id": "010b087db4d3304e9e071089d3b46b37" } ]
5531e115d677b2e2c286de4c80d2020a
c47a14e8cef4d702f537d32cadf8a5d4
“… አፈር ስሆን !”
 ጠረጴዛ ሙሉ ምግብ በአይነት በአይነቱ ደርድረን ‹‹ኧረ ብሎ! ምነው ብሉ እንጂ በሞቴ! … አፈር ስሆን!›› ብሎ ለምኖ የሚጋብዝ ሰው ከኢትዮጵያውያን ውጪ የትም አገር ላይ ያለ አይመስለኝም:: ይሄ የኛ ማንነት ነው:: ‹‹እንዲያው ለምዶብን ነው ›› እንዳትሉኝ እንጂ እኛ ኢትዮጵያውያን ከሌላው ዓለም የምንለይበት ብዙ ባህሎችና ልምዶች ያሉን ህዝቦች ነን:: መዘመን ሳይከፋ አሁን አሁን ያለ ባህል ወጉ ፈር የለቀቀ ስልጣኔ አለኝ ባዩ በዝቶ ካልሆነ በስተቀር፤ የሚያምርብን ወጉ አብሮ መብላት መጠጣቱ ነው:: ምክንያት ፈልገው አብረናቸው እንድንሆን የሚሹት ቤተሰቦቻችን:: ወላጆቻችን:: ጎረቤቶቻችን:: ጓደኞቻችን… ቤታቸው እስክንሄድ ጉጉቱ ሊገላቸው ነው የሚደርሰው፤ አግኝተውን ነው:: ፍቅር አስገድዷቸው ያለ የሌላቸውን ሁሉ አቅርበው ‹‹ኧረ አፈር ስሆን!›› ይሉናል:: አፈር ስሆን ብሎ ለሚጋብዝ ወዳጅ በወጉ በባህሉ ‹‹ኧረ ጠላትሽ! ለምን አፈር ትሆኛለሽ/ትሆናለህ›› ብለን ቤት ያፈራውን መመገብ ነው፤ እየተገባበዙ መተሳሰቡ:: ያን ጊዜ አቤት ጨዋታው መድራቱ፤ በተለይ ኢትዮጵያዊ ወጉ። እስኪ የዚህን ዘመን የኑሮ ውድነቱን አስቡት። ከዚያ መልስ ወግ ባህላችንን። እውነት ዘመኑ ያገባብዛል? እንዳለው የኑሮ ውድነት፤ ዶሮ በአራት መቶ ብር ገዝቶ ማለቴ ድሮ ሰንጋ በሚጎተትበት ብር። ምን አራት መቶ ብቻ ዶሮ ከነልጆቿ ከነማጠፈጫው የአንድ ሺ ብር ጌታ ሆና ሰው ሁሉ በሩን ዘግቶ መብላት አልነበረበትም ትላላችሁ? ነገሩ ግን ወዲህ ነው። እኛ ኢትዮጵያውያኖች ነን።ባህላችን አይፈቅድም። በር ዘግተን አንበላም። ኑሮ ለምን ከፈለገ ጣሪያ አይነካም። የምን ሰስቶ ቆንጥሮ መመገብ ነው። የኛ ማንነት ይሄ በመሆኑ በራችንን ከፈት አድርገን ‹‹ግቡ… ግቡ ጎራ በሉ:: አረፍ በሉ›› እንላለን። ወዲያው ይከተላል ከምግብ ከመጠጥ በአይነት በአይነቱ። ያቀረብነውን ማእድ እንግዳ እያማረጠ ሲበላ እያየንም አንረካም፤ እንቀጥላለን ‹‹ኧረ ብሉ! አፈር ስሆን… በሞቴ!››። ደስ ብሏቸው እንዲመገቡት ከምግቡም ቀመስ እያደረግን ‹‹ጣፋጭ ነው ‹‹በባለሙያ የተዘጋጀ ነው›› እንላለን። ምክንያቱም እኛ ኢትዮጵያውያን ነን። ብርጭቆውን ሞልተን ቀድተን ወደ አንደኛው የእጃችን መዳፍ ከመጠጡ ፈሰስ እያደረግን ‹‹እንዴት ጥሩ ጠላ›› የማር ጠጅ መሰሎት፤ ጠጁ በቤት የተዘጋጀ ነው ፤ ጠላው ገብስ ? ለስላሳ ጉሽ ነው እራስ አይነካም›› እያልንም ለጤናም ዋስትና እንሰጣለን። ባህል ወግ መከባበራችንን እናሳያለን። ሁሉም እንዲበላልን፤ እንዲጠጣልን በመጓጓት። አቤት ሲያምርብን ምክንያቱም ባህላችን ነዋ። ያለውን ሁሉ በአይነት በዓይነቱ አቅርቦ ብሉልኝ በሚል ተማጽዕኖ አድርጎ ብቻ የሚረካ ጥቂቱ ነው። ይሄ ነው የእኛ ባህላችን ግቡልኝ ብሉልኝ ጠጡልኝ ማለታችን። ያለውን ተካፍሎ ተቋድሶ መመገብ ፤ደግሞ መመራረቅ ‹‹ለከርሞ በሰላም ያድርሰን›› ብለን ለቀጣዩ ዓመት መልካም ተመኝተን ‹‹ለሰጫችን ይስጥልን›› ብለን እንለያያለን። እኛም ተራ አለንና ልንጋብዝ እንዘጋጃለን። ይሄ የእኛነታችን ባህል ታዲያ ከወንዝ ወዲህና ከወንዝ ወዲያ አይልም። ብሄር? ቋንቋ? ፆታ? ቀለም? አይጠይቅም። ኑ አብረን እንብላ እንጂ ‹‹አንተ ቆይ ከብሄርህ ጋር ተቀላቀል›› የተባባለበትን ዘመን እኔ በበኩሌ አላስታውስም። ኧረ እንዲያውም የለም። ሁሉም ሰው ጓዳው ሲሞላ በዓል ሲመጣ በአንድ ገበታ መቋደሱ የነበረ ነው። አሁንም ያለ ወደፊትም አጠናከረን የምንቀጥለው። የትም እግራችን እስኪቀጥን ሄደን የማናገኘው ኢትዮጵያዊ ባህላችን ነው። መታወቂያችን! ስለኛ ብዙ ካልኩ አይቀር ባህል ወጋችን ልዩ የሚያደርገን ውብ ማንነታችን መሆኑን ለማሳየት እስቲ አንድ ትዝታዬን ላውጋችሁ። ባህር ማዶ አንድ ወቅት ብቅ ባልኩበት ጊዜ የገጠመኝን ነበር። ሁሌም አስታውሰዋለሁ። ደቡብ አፍሪካ ነው። በቆይታዬ አገሪቷን ከባልደረቦቼ ጋር ዞር ዞር ብለን ከጎበኘን በኋላ ሰብሰብ ብለን እራት ለመመገብ ወደ አንድ ምግብ ቤት ገባን ። እኛ ካዘዝነው ምግብ በቁጥር እንበልጥ ነበር። ከሰው ቁጥር በአንድ የሚያንስ ምግብ አዘዝን። ማይነስ ዋን እንደሚባለው ማለት ነው። አስተናጋጁ ግን ‹‹አንድ ሰው ያላዘዘ አለ›› በሚል ደጋግሞ እንዲታዘዝ ጠየቀ። አንዱን ምግብ ለሁለት ልንመገበው መሆኑ ሲነገረው በጣም ግር አለው። ኧረ እንዲያውም ገረመው። ይህን አይነቱን ባህል አያውቅምና የታዘዘው አይነት ተጨማሪ ምግብ እንዲመጣ የተነገረው መስሎ ተሰማው። አሁንም አለመሆኑ ተነገረው። ሲመለስ ግን ‹‹ማንም የማንንም ምግብ መመገብ እንደማይችል ፤ ያዘዘውን ምግብ በልቶ ካልጨረሰ ደግሞ አስጠቅልሎ በቴክ አዌይ መልክ አስደርጎ ወደ ቤቱ መውሰድ አለበት›› በማለት ሊያስረዳን ሞከረ። የሆቴሉ ህግም ሆነ የእነሱ ባህል ሁሉም የራሱን ይበላል እንጂ የሌላውን መካፈል አይችልም የሚል አይነት ነበር። እኛም ተገረምን እነሱም ደነቃቸው። አንድ ሰሀን ላይ በጋራ መመገብ። ለዚያውም እየተጎራረሱ መመገብ ለለመደ ሰው ይሄ በጣም እንግዳ ሊሆን ይችላል። በእኛም ላይ ይሄ ነበር የተፈጠረው። በአንድ ገበታ ላይ ከአምስት ያላነሱ እጆች ተዘርግተው እንደ ፍላጎታችን ጠቅለል አድርገን በመጉረስ ካለማንም ገሳጭ የምንበላው ምግብ ነው። አንድ ምግብ ለሶስት ብንበላስ ማን ከልክሎን። በወቅቱ የሌላውን እና የራሳችንን ባህል እያነፃፀርኩ ተገረምኩ ። አጋጣሚውን ግን የጨዋታ ማድመቂያ አድርገነው ምግባችንን አወራረድን። ‹‹ኧረ ብሉ አፈር ስሆን›› እየተባለ ምግብ ከሚጋበዝበት አገር የመጣን እንግዶች፤ ኢትዮጵያውያን መሆናችንን አላወቀምና አይፈረድበትም። መለስ ብዬ ኢትዮጵያዊነት አስተዳደጋችንን ሳየው አሁንም እኮራለሁ። ቤተሰቦቻችን አንድ በሬ ለአስር ተካፍለው ቅርጫ አብልተውናል። እኛም ዓመት በዓል በመጣ ቁጥር ቅርጫ የለም እንዴ ብለን በጉጉት እንጠብቃለን። የስጋ አምሮታችንን የምንወጣው በጋራ ከምናርደው የዓመት በዓል በሬ ነው። ከልጅነት አእምሮ የማይረሳው አንዱ ቅርጫ ነው። አባቴ ወደ ቅርጫው ቦታ በማለዳ የሚያመራው ‹‹ረፈድ ሲል ዘንቢል ይዛችሁ ኑ›› የሚለውን መልዕክቱን አስቀድሞ ነው። እኛስ ብንሆን አዲሱን ቀሚስ ለማስመረቅ ከጓደኞቻችን ጋር ለመገናኘት ያ ጥሩ አጋጣሚ አይደል? ከተባላው ሰዓት ቀደም ብለን ተጠራርተን ዘንቢል አንጠልጥለን በበሬ ማረጃው ስፍራ ከተፍ ነው። ልጆች አንዳንዴም ሴቶች ዘንቢላቸውን ይዘው ዳር ላይ ቁጭ ብለው ይጠባበቃሉ ምኔ በደረሰ እያሉ። ወንዶቹ ከዚህ ወደዚያ ተፍተፍ ይላሉ። አባቶቻቸውን ይረዳሉ። የእርድ እና የመከፋፈሉ ስራ ሳይጠናቀቅ እንጀራ በትሪ‹› አዋዜ እና ሚጥሚጣ ከች ይላሉ። አዋዜው ካልደረሰም ችግር የለም በርበሬው በአረቄ ተለውሶ አዋዜ ይሆናል። ይሄኔ በስፍራው የተገኘው ሁሉ ጉበት ማወራረድ ላይ ይሳተፋል። ‹‹ግሩም ነው›› ከሚለው ጀምሮ ‹‹ጉበት እኮ ለደም ማነስ ፍቱን መድሃኒት ነው›› እስከሚለው የጉበት ጠቀሜታ ተንታኝ ሆኖ ቁጭ ይላል። ከጉበቱም ከቁርጡም በሚጥሚጣ እየተለወሰ በስራ ለተጠመዱት ከስር ከስር ጉርሻው ይካሄዳል። ወባ እንደያዘው ሰው የሚንቀጠቀጠውን ትኩሱ የበሬ ስጋ እየቆራረጡ መመደቡ ምን ያህል ፍትሀዊነት እንዳለው አስቡት ። በእያንዳንዱ ሰው ላይ ያለው እምነት ሙሉ ነው ።ሚዛን አይጠየቅ፤ የሀይማኖት አባት ወይም ሽማግሌ አይጠራ ብቻ በራስ እጅ ? በአይን ሚዛን እጅ እንዳመጣው ይመደባል። ድልድሉ ሲያበቃ አነስ ያለ ልጅ ይጠራና በወረቀት ላይ ተፅፎ የተጠቀለለውን ስም በየመደቡ ላይ እንዲያስቀምጥ ይደረጋል። ያኔ በቃ ተመራርቆ ምድቡን ማንሳት እንጂ የእከሌ ትልቅ የአያ እከሌ ትንሽ የሚል ፈፅሞ አይነሳም። ከዚህ ብሄር ከዚያ ፆታ ብሎ የሚከፋፍል ቀርቶ በሀሳቡ የሚመጣበት የለም። በጊዜው የቅርጫ እንጂ የብሄር ክፍፍል የማይታሰብ ነው። አንድ በሬ ለአስር ቤተሰብ፤ በአንድ ቤተሰብ አምስት ሰው ቢኖር፤ አንድ በሬ ለሀምሳ ሰው በፍቅር ተካፍለን እንበላለን። ደግሞ እንመራረቃለን፤ ለቀጣዩ ዓመት በሰላም? በደስታ ? በጤና ያገናኘን ብለን። ምክንያቱም እኛ ኢትዮጵያውያን ነንና። ሁላችንም ጎረቤታሞች ስጋውን ተካፍለናል ፤በሁሉም ሰው ቤት ስጋ አለ፤ ስጋ የምለው ለእኛ ትልቁ ክብርም የምንሰጠው ምግባችን ስለሆነ እንጂ በዕለቱ ጠላው? ጠጁ? ዳቦው? ፈንድሻው ? ቡናው… ሁሉ ሳይቀር በእያንዳንዳችን ቤት አለ። ምን ቢሞላ ያለ ሰውና ካለ ጎረቤት አይጥምም። ስለዚህ ‹‹ኑ ቡና ጠጡ›› እንላለን። አብሮ የበላና አብሮ የጠጣ በሀዘን በደስታውም አይተጣጣም እንደማለት ነው ። እናም ምሳ አንዱ ቤት፤ እራት ሌላኛው ቤት። አብሮ ይጫወታል ፤አብሮ ይደሰታል ይሄ ሀሳብ የምንለዋወጥበት መድረክም ነው። የተጣላ ማስታረቂያም ነው። መቼም ከሰው ጋር በተለያየ ምክንያት መጋጨቱ አይቀሬ ነው። በልጅም በውሻም፤ በሌላውም በሌላው ብቻ የጠብ ምንጭ አይጠፋም። ግን ፀቡ አይዘልቅም። ቢሆንም ግን ዘር ማንዘር፣ ብሄር ብሎ አይቆጠርም። ‹‹እገሌና እገሊት ተቀያይመዋል›› ከሚል አያልፍም። ለዚህ ደግሞ ‹‹በዳይ ተበዳይ›› ተለይቶ ይቅርታ እንዲጠያየቁ ይደረጋል። የይቅርታው ማሳረጊያም አብሮ መብላት ይሆናል። አብሮ የበላ ጥርስ አይሳበርም፤ ሰላም ለመንደሩ፤ ሰላም ለቤተሰብ፤ ሰላም ለሁላችን ይሆናል:: ይሄ ነው ኢትዮጵያዊነት ባህላችን። አብሮ በልቶ፣ አብሮ ጠጥቶ፣ ሲጣሉ ታርቆ፣ ደስታና ሀዘንን በጋራ ተካፍሎ ማሳለፍ። ታዲያ ይሄ ሆኖ ስር መሰረታችን፣ ማንነታችን፤ ዛሬ ላይ በሆነው ባልሆነው መጎነታተሉን ምን አመጣው? በሉ እንግዲህ መቼም ‹‹ችግር አይፈጠር›› ሳይሆን ሲፈጠር ባሉን ባህላዊ እሴት ማረቅ እንደምንችል መረዳት ነው ዋናው ቁምነገሩ። ኑ ማዕድ ዳር እንሰባሰብ! መጎነታተሉን ተወት አድርገን ‹‹እስቲ በሞቴ አፈር ስሆን…..ብሉልኝ ጠጡልኝ›› እያልን አብሮነታችንን እናድስ:: ሰላም!አዲስ ዘመን መስከረም 4/2012 አልማዝ አያሌው
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=18056
[ { "passage": "የሀገራችን ሰዎች ስለዝንጀሮም ሆነ ጦጣ ብልጠት መተረክ፤ መዝፈንና መጫወት ይወድዳሉ፤ ስለ ሁለቱም «ገዳይ ገዳይ አለች የቆለኛ ልጅ፤ አባቷ\nምን ገድሏል? ዝንጀሮ ነው እንጂ» ተብሎ ይዘፈናል። «ዝንጀሮ በዳገት ጦጣ በዛፍ ላይ፤ የማይበላ እህል\nይጠበቃል ወይ» ይባላል። ይህ ዘፈን ተፈልጋ በቀላሉ የማትገኝን ፍቅረኛ ተስፋ ማድረግ ከንቱ እንደሆነ ይመክራል። «የዝንጀሮ ባልቴት አትባልም አንቱ፤ ላርግሽ በደረቴ እንዳበደ ሴቱ\n። ዝንጀሮ ጠባቂ\nላያድር ያመሻል፤ ፈርቼሽ ነው\nእንጂ ልቤ ከጅሎሻል» የሚል ዘፈንም አለ። አበደ\nሴቱ የተባለው ሴቶች ሁሉ የወደዱትና ያበዱለት የአንገት ጌጥ (ግማዴ) ሊሆን ይችላል። የዝንጀሮ ባልቴት በአንቱታ እንደማትጠራ አንቺም እኩያየ ነሽና በደረቴ ላይ ላርግሽ፤ ልለጥፍሽ እንደማለት ነው። «ዝንጀሮ እንኳን ባቅሙ ያውቃታል ወዳጁን፤ የፈለፈለውን ይሰጣታል የጁን»\nተብሎም ተዘፍኗል። የባለሥልጣኖች የሙስናና የዘረፋ ነገር\nሕዝቡን ስለአማረረው «የጅብ ሊቀ መንበር፤ የዝንጀሮ ዳኛ፣ የጦጣ ጸሐፊ፤ ሁሉም\nሌቦች ናቸው አታላይ ቀጣፊ» ተብሎ መዘፈኑም ይታወሳል። በተረትም ዝንጀሮ ሲጠግብ ያባቱን ዋሻ ይረሳል ይባላል። ጦጣን አስመልክቶ «ጦጣ ባለቤቷን ታስወጣ» ሲባልም መስማት የተለመደ ነው። በዝንጀሮና ጦጣ ላይ ለመንደርደር የፈለግሁት በቦኩ መካነ ጸበል ቆይታየ የታዘብኩትን ላካፍላችሁ ፈልጌ ነው። ቦኩ ከአዳማ ከተማ ምሥራቃዊ ክፍል በግምት አምስት ኪሎ ሜትር ያህል ርቆ የሚገኝ ስፍራ ነው። ጥቅጥቅ ያለ ደን ያለበት፣ የተፈጥሮ እንፋሎት የሚፈልቅበትና ዝንጀሮ፣ ጦጣ፣ ጅብና ሌሎች የዱር እንስሳት የሚፈነጩበት ድንግል የተፈጥሮ አካባቢ ነው። ከቦኩ ገደላማ ቦታ ላይ ሆኖ ቁልቁል ሸለቆውን፣ ገጸ ምድሩን፣ ልዩ ልዩ የዛፍ ዓይነቱን ሲመለከቱት መንፈስን ያድሳል። በአጭር ርቀት አረንጓዴ የሆነውን የወንጂን የሸንኮራ አገዳ ተክል በሠፊው ሜዳ ላይ ተዘርግቶ ሲያዩት ልብን በተስፋ ያለመልማል። ቀደም\nባለው ጊዜ ታላላቅ ሰዎች ሳይቀሩ በቦኩ የተፈጥሮ ደን ውስጥ በመገኘት የአደን ሥነ ሥርዓት ያካሂዱበት ነበር። በጤና እክል ምክንያት ወደ ቦታው ሄጄ በነበረበት ሰዓት መምህሬ ጀንበሬ ብዙ ወርቅ የተባሉ የእንፋሎቱ ደንበኛና ቋሚ ተጠቃሚ እንዲሁም የመቂ ከተማ ነዋሪ የሆኑ አዛውንት እንዳጫወቱኝ፤ የቀድሞው ንጉሥ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ በደጃዝማችነታቸው ዘመን ከነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ጋር ወደ ሥፍራው በፈረስ እየሄዱ ድኩላና ሌሎች የዱር እንስሳትን ያድኑ ነበር። ደጃዝማቹ አደን በሚያድኑበት ሰዓት ከቦኩ ገደል ሥር እንደ ጭስ እየተነነ የሚወጣውን የተፈጥሮ እንፋሎት ይመለከታሉ። ይህ እንፋሎት የሕዝብ መታከሚያ እንዲሆን በማሰብ በነጋድራስ ተሰማ እሸቴ እንዲጠና ካደረጉ በኋላ እንዲመሠረት ያደርጋሉ። መምህሬ ጀንበሬ እንዳጫወቱኝ ያኔ የ27 ዓመት ወጣት ነበሩ። በተፈጥሮ እንፋሎቱ ለመጠቀም በ1947 ዓ.ም ወደ ቦኩ ሲሄዱ ለጸበልተኞች ማረፊያ ትንሽዬ ሣር ቤት በመሠራት ላይ ነበረች። የሣር ቤቷ ግድግዳ ቆሞ ሣር ከዳኝ ይጠፋል። እርሳቸውም ዕውቀቱ ስለአላቸው “እኔ ልክደነው” ብለው በቀን 1.50 ሳንቲም እየተከፈላቸው ቤትዋን አሳምረው በሣር ክፍክፍ ይከድኑዋታል። በወቅቱም በአካባቢው የነበሩ ነዋሪዎች ጠላ፣ ቆሎ እንጀራ፣ ዳቦ፣ ለጸበልተኛው ያቀርቡ ነበር። ያኔ ዝንጀሮዎችና ጦጣዎች ራቅ ብለው ድርጊቱን በጨዋነት ከመመልከት በስተቀር እንዲህ እንደዛሬው ዓይን ያወጡ ዋና ተዋናዮች አልነበሩም። በወቅቱ የተፈጥሮ እንፋሎቱ የቦኩ ሚካኤል ጸበል እየተባለ ከመጠራቱም ባሻገር ሰው በተለምዶ የእንፋሎት መታከሚያ ክፍሎችን ገብርኤል፣ አቦ፣ ማርያም እያለ ይጠራቸው ነበር። በኋላ ላይ የተፈጥሮ እንፋሎቱ ከእምነት በተላቀቀ መልኩ ለሁሉም የእምነት ተከታዮች መታከሚያ እንዲሆን ስለታሰበ የየትኛውም እምነት ተከታይ ይገለገልበታል። የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች በቆርቆሮ እንዲሠሩ ተደርጐ አገልግሎት ሲሰጥ በነበረበት ሰዓት አንድ ባለሥልጣን ታክመው ስለዳኑበት መብራት እንዲገባለት እንዳደረጉ መምህሬ ጀምበሬ አውግተውኛል። የቦኩ ሚካኤልም ከአካባቢው ተነሥቶ ከዋናው አዳማ ከተማ መግቢያ በር ላይ በዘመናዊ ፕላን ቤተክርስቲያኑ በካቴድራል መልክ እንዲገነባ ተደርጓል። ከአንዳንድ ሰዎች እንደተረዳሁት የተፈጥሮ ሀብቱን መንግሥትም፣ ግለሰብም ሲያስተዳድረው የቆየ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ዲንሾ የተባለ ድርጅት ተረክቦ፣ ዘመናዊ የእንግዳ ማረፊያ ቤቶችን፣ የአልጋ ክፍሎችን ካፊቴሪያዎችን ገንብቶ ለተጠቃሚዎች አገልግሎት ከመስጠቱ ባሻገር እንግዶች እንዳይጉላሉ ከአዳማ ቦኩ አድርሶ የሚመልስና በየቀኑ የሚመላለስ ተሽከርካሪ መድቦ የሕዝቡን ችግር አቃልሏል። በተለይ ለ1ኛ ደረጃ የእንፋሎት ክፍሎች ተጠቃሚዎች የዘመናዊ ሻወር አገልግሎት እንዲያገኙ አድርጓል። የውኃ ማጠራቀሚያ ታንከርም አዘጋጅቷል። ዘመናዊ የእንፋሎት መገልገያ ክፍሎች ኃይለኛ የሙቀት መጠን በማመንጨታቸው ምክንያት ተጠቃሚዎች በተለምዶ “ጥቁር አንበሳ”፣ “ፌዴራል ፖሊስ”፣ “መከላከያ”፣ “ጤና ጥበቃ”፣ ትምህርት ሚኒስትር” ብለው ይጠሯቸዋል። በዚህ ዓይነት በጣም የሚጋረፈው እንፋሎት በአሁኑ ጊዜ ፌዴራል ተብሏል። ፌዴራል ገብቼ ወጣሁ ይባላል።በደረጃ በተከፋፈሉት የተፈጥሮ እንፋሎት መገልገያ ቦታዎችም ሰው ደስ ብሎትና በጥሩ ሁኔታ ተስተናግዶ ወደመጣበት ይመለሳል። በተለይ የመታጠቢያ ውኃ በባልዲ የሚያቀርቡና ክፍሎቹን ሰው ተጠቅሞ በወጣ ቁጥር አጽድተው ለአገልግሎት የሚያዘጋጁ ወጣቶች ታታሪነት በእጅጉ ያስደንቃል። ነገር ግን በቦኩ የእንፋሎት መገልገያ ቦታ ጧት፣ ሌሊትና ማታ አካባቢውን መድፍ የተተኮሰ ያህል የሚያናውጠው የጅብ ጩኸት፣ ስልት ያለው የዝንጀሮዎችና የጦጣዎች ቅሚያና ዘረፋ አያድርስ ያሰኛል። መንገደኛ ገና ከመኪና ሲወርድ የቦኩ ዝንጀሮዎችና ጦጣዎች እጅብ ብለው ወደ ሰው ሲመጡ መልካም አቀባበል ለማድረግ ያሰቡ ይመስላሉ። መንገደኛው አገልግል፣ ፌስታል፣ ሻንጣ፣ ሊያንጠለጥል ይችላል። እነ አጅሬ ያዩትን ነገር ከመቅጽበት ላፍ አድርገው ይሮጣሉ። በየመኝታ ክፍሉም እየገቡ ይዘርፋሉ። ምግብ፣ ሙዝ፣ ብርቱካን፣ ሞባይል፣ ልብስ በፌስታል… የተያዘ ነገር ነጥቀው ይሮጣሉ። አልጎረስ፤ አልነከስ ያላቸውን ሞባይል ወደ ገደል ይወረውሩታል። እነዚህ ማጅራት መቺዎች የካፊቴሪያና የአልጋ መስተዋቶችን ሰባብረው ጥለዋቸዋል። በተለይም ካፊቴሪያዎች ኮርኒስ ስለሌላቸው ጦጣዎች ተንጠልጥለው ይገቡና ከወራጁ ላይ ይሠፍራሉ። ምግብ በሚቀርብበት ሰዓት ከላይ ሆነው ሽንታቸውን በምግቡ ላይ ይለቁታል። ሊበላ ያሰፈሰፈ ሁሉ፤ “አይ አይ አይ” በማለት ምግቡን ወደ ውጭ ሲደፋው ተንደርድረው በመውረድ እየተሻሙና እየተጣሉ ይበላሉ። የዝንጀሮ መንጋው ሰላማዊ መስሎ እየተጐማለለ በካፊቴሪያ ዙሪያ ይሠፍራል። ያላወቀ ሰው ምግብ አዝዞ ሊበላ ሲል መስተዋቱ በረገፈው ግድግዳ በኩል እጁን ልኮ ከመቅጽበት ምግቡን ይዞት ይሮጣል። አንዲት ሴትዮ ከመኪና እንደወረዱ እንጀራ በአገልግል ታቅፈው ሲራመዱ፣ አንድ ትልቅ ግመሬ ዝንጀሮ ትልቁን አገልግል በቅጽበት ላፍ አደረገና ወደ ላይ ወደ ገደሉ ይዞት ወጣ። ወዲያው አገልግሉን ፈታታና ለሳምንት የተያዘውን ስንቅ በደቂቃ ውስጥ ብቻውን ጠብ አደረገው። ከዚያ ቆየና አገልግሉን ወደታች ሲወረውረው አገልግሉ ተንከባልሎ በእልህና በንዴት ሲንጨረጨሩ ወደነበሩት አሮጊት ዘንድ ደረሰ። “ተመስጌን እንኳን አገልግሌን ሰጠኸኝ” ብለው ዝንጀሮውን አመሰገኑት። የዱር እንስሳቱን ብልጠት ሰው ሁሉ እንደ መዝናኛ ከመመልከት ውጪ የሚጨክንባቸው የለም። የዝንጀሮ እና የጦጣ መዛለያ የሆኑት የጣሪያ ቆርቆሮዎች ተጣመዋል፣ ረግበዋል። በቦኩ አካባቢ ያሉ ዝንጀሮዎችና ጦጣዎች ከሰው ጋር ማኅበራዊ ኑሮ ስለመሠረቱ የዕለት ምግባቸውን ለማግኘት ወደ ጫካ ከመሠማራት ይልቅ እየቀሙ መኖርን ተለማምደውታል። ሰው መፍራትም ማፈርም ትተዋል። የሶደሬ ጦጣዎችም ልክ የቦኩ ዘመዶቻቸው እንደሚያደርጉት ኑሯቸው የተመሠረተው በንጥቂያ ላይ ነው። የቦኩ ጦጣዎች ከንጋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ይርመሰመሳሉ። ዝንጀሮዎች ግን በአብዛኛው 4 እና 5 ሰዓት ላይ በብዛት ከወጡ በኋላ በ11 ሰዓት\nወደ ሠፈራቸው ይከትታሉ። የመንገደኛ ዳቦና አምባሻ የለመዱትና በዓባይ በረሃና ጊቤ በረሃ ውስጥ የሚኖሩት ዝንጀሮዎችና ጦጣዎች ግን ጨዋነት ይታይባቸዋል። መኪና ባለፈ ቁጥር እጃቸውን እያውለበለቡ ከመለመን መኪናውን አላሳልፍ ከማለት ውጪ ከሰው አይቀሙም ። በነገራችን ላይ ዝንጀሮም ሆነ ጦጣ ከሰው የሚሻሉበት መንገድ አለ። ቆየት ያለ አንድ ጥናት እንዳረጋገጠው፤ ዝንጀሮ ከሕጋዊ ሚስቱ ውጪ ወደ ሌላ ሄዶ አይወሰልትም። ሚስቱ ብትሞትበትም ወይንም ሚስት ባል ቢሞትባት “ይመነኩሳሉ” እንጂ ሁለተኛ ጋብቻ አይፈጽሙም። ጦጣዎችም እንዲሁ ናቸው። ነውረኝነታቸው ግን በዚያ ሁሉ ሕዝብ መኻል የወንድና የሴት ግንኙነት መፈጸማቸው ነው። ሌላው ወንድ ዝንጀሮ ሽንቱን ከሸና በኋላ ብልቱን በእጁ ይዞ ሽንቱን ማራገፉ ለንጽሕናው ያለውን ትኩረት ያመለክታል። በቦኩ ቆይታዬ\nአንድ ጅብ ከጧቱ\n3 ሰዓት ገደማ አጠገባችን\nጩኸቱን እንደ መድፍ\nለቅቆ ቢያስደነግጠንም ግቢው\nበታጣቂዎች በሚገባ ስለሚጠበቅና\nአጥሩም የተጠናከረ በመሆኑ\nየፈራ ሰው አልነበረም።\nይልቁንም ጸበልተኛው ሁሉ እየሣቀ\n“አይ አጅሬ ጠብቶበት\nሳይሆን ረፍዶበትኮ ነው ምድሩን\nበጩኸት የሚያናውጠው» እያለ\nተዘባበተበት።አዲስ ዘመን ግንቦት 2/2011 በ", "passage_id": "cb30eef524f4bb6999ed5b4ec41d267a" }, { "passage": "ዝቅ ማለት ከፍታ ላይ ያደርሳል እንዴ? አንድ ዓረፍተ ነገር ሰምተነው ግራ የሚያጋባን ጉዳይን ከመግለፅ በላይ የሆነን ቁም ነገር የጨበጠ ሆኖ ስናገኘው መመርመር እንጀምራለን። ከፍታ ላይ ለመገኘት ዝቅ ብሎ መጀመር የተሻለ ቦታ ላይ ለመገኘት ቀድሞ የሚያሽልን መጠጋት ግድ ይላል። በነገራችን ላይ ውዶቼ ለማትረፍ ተብሎ ካለ ላይ መቀነስ መሰጠትን ይጠይቃል። ሁሉም እኮ የመስጠት ጣዕምን አይረዳም።\nእራስን አሸንፎ ከስግብግብነት መላቀቅን ከራስ ወዳድነት ስሜት መመንጨቅን ይጠይቃል። ይህ ደግሞ በመሰጠት ውስጥ ባለ መልካምና እራስን\nከሌላው ቀጥሎ ማየትን ቀድሞ ከራስ ሌላ መኖርን ይፈጥራል። አቤት የዚህ ስሜትና ተግባር ጣዕሙ። እራሱን ለሌሎች ደስታ ምክንያት\nበመሆን ጣፋጭ የሆነን ደስታ ማግኘት ምንኛ መታደል ነው።እኛ ጋር ያለ ውዳቂ ነገር ሌሎች ጋር\nየማይገኝና ውድ መሆኑ የማናውቅ ብዙ ነን። እኛ ተርፎን የምነደፋው ምግብ ብዙዎች ሽታው እንኳን እንደራቃቸው የማናስተውል በዝተናል።\nእያለን መስጠትን ካለመድን ስናጣ መቀበል እናውቅበት ይሆን እንዴ? የማይሰጡ እጆች መቀበል ይከብዳቸዋል። መስጠት ቁስን ብቻ አይደለም።\nበጎ ሐሳብ የሚለውጥ ሃሳብ አገር እና ሰውን ሊያቆም የሚችል ሁነኛ በጎ ተግባርም መስጠትን ይገልፃል። በእርግጥ መስጠት ከመቀበል ቢልቅም\nበመስጠት ውስጥ የሚገኘው መንፈሳዊ ጠቀሜታ ተቀባይ ባልጠፋ ያሰኛል። እያለን መስጠትን የራቅነውን ያህል ስናጣ የምንቀበለው ይርቅብናል።\nመስጠት ለመልመድ ከሌለው የሚሰጥ ካጠረው ላይ ቆርጦ ለሌላ የሚለጥፍ ስናይ እራሳችንን እንድናይ እኔስ ምን ላይ ነኝ? ያለሁት የሚል\nጥያቄ እንድናነሳ ያደርገናል። ካለ ላይ መስጠት የሚቀለው ያህል ከሌላ ነገር ላይ ቀንሶ እንካችሁ ማለት ይገዝፋል። ከሌለ ላይ መስጠት\nከባድ ነው፤ ነገር ግን መስጠት ያለው ፋይዳ ላወቀ ይገዝፍበታል። የበጎ ተግባር ያህል ውስጥን ሰላም የሚያስገኝ፤ የመልካም ሥራ\nያህል ውስጥን የሚያድስ ተግባር ከወዴት ይገኝ ይሆን? አንዳንዱ ሰጥቶ የማይጠግብ፣ በጎ ምግብር አድርጎ የማይሰለች ለሰው ኖሮ የማይደክም\nየሆነው የመስጠትን ጣዕም በደንብ ስለገባው ነው።እርግጥ መስጠት ወይም ደግነት እኛ ኢትዮጵያዊያን የማንታማበት ጉዳይ ሆኖ አብሮን ከርሞ አሁን ላይ\nያረጀብን ቢመስልም የበጎነት እርጅና ወደ ሞት እንዳያመራ በአንዳንድ ተንከባካቢዎች ዛሬም ፈክቶ ይታያል። እዚህች አገር ላይ በበጎነት\nስማቸው የናኘ በደግነት ትልልቅ ምግባሮችን የፈፀሙ ኢትጵያዊያን መርሳት ይከብዳል። ደጋግ ልቦች ደጋግ ነገሮች ሁሌም ያሳያሉ። ሰሞኑን በማህበራዊ ገፆች አንድ ጉዳይ ብዙዎች ሲቀባበሉ አንዳንዶችንም ልብ የነካ ተግባር በአንድ\nኬኒያዊ የጎዳና ተዳዳሪ ከሌለው ላይ በመቀነስ ለሰው ህይወት መትረፍ ምክንያት ስለሆነ ታደጊ የተሰራጨው መረጃ በእርግጥም የደግነት\nጥግ የበጎነት ያልተገደበ ድንበር ያመላከተ ነበር። ጉዳዩ እንዲህ ነበር። ምስኪኑ የጎዳና ተዳዳሪ የሰራው ድንቅ ሥራ ይህ ነበር።\nስሙ ጆን ይባላል። የዕለት ጉርሱን ለምኖ በረንዳ የሚያድር ምስኪን ህፃን ነው። ታዲያ ጆን አንድ\nዕለት እንደለመደው ትራፊክ መብራት ላይ መኪኖች ሲቆሙ በመስኮት ሄዶ መለመኑን ተያያዘው። ከበርካታ መኪኖች ገንዘብ ተቀብሎ ወደ\nአንዱ መኪና በመስኮት እጁን ይዘረጋል።ለዚህ ታሪክ መከሰት ዋንኛ ጉዳይም ይሄው ለዕርዳታ የዘረጋው እጁ ያስከተለው ጉዳይ ነበር።ህፃኑ ጆን እጁን ሲዘረጋ የመኪናው መስኮት ሲከፈት ግላዲ ካማዳ ከተባለች ሴት ጋር ፊት ለፊት ይተያያል።\nህፃኑ አንድ ነገር ያያል እናም ግላዲ ካማዳ ያረገችውን የኦክስጅን መተንፈሻ “ምንድነው?” ብሎ ይጠይቃታል። እሷም በሰው ሰራሽ\nመተንፈሻ ኦክስጅን የምትተነፍስ አይኗም በቅጡ የማያይ በእግሯ መንቀሳቀስ የማትችል በየዕለቱ ጤና ፍለጋ ሆስፒታል የምትንከራተት\nመታከሚያ ገንዘብ ያጣች 7 ዓመት ሙሉ በዚህ በሽታ የምትሰቃይ ምስኪን ሴት መሆኗን ትነግረዋለች። ይህንን ያየው የጎዳናው ህፃን ጆን እንባውን መቆጣጠር አቅቶት ለልመና የዘረጋውን እጁን ሰብስቦ እጁን\nዘርግቶ ከሌሎች ያገኘውን ጥቂት ገንዘብ ታከሚበት ብሎ ይሰጣታል። እንባውና ሁኔታው የገረማቸው መንገደኞችም በሁኔታው ተደንቀው የልጁን\nየሃዘን ገፅታ በምስል አስቀሩት። በዚህም አላበቃም የህፃኑ ምስል በፌስቡክ ይለቁታል። ከፎቶው ጋር አብረው ልጁ ምን አይቶ እንዳነባ\nበምን ልቡ እንደተነካ ጽፈው ፎቶውን ያጅቡታል። ድፍን ኬንያ ይህንን ምስል ተቀባበለው። ሁሉም የልጁ ሐዘን አሳዘነው። ይህ ልጅ ምንም ሳይኖረው የዳቦ\nመግዣውን ከሰጠ እኛስ? የሁሉም ጥያቄ ሆነ። ስለ ጉዳዩ ተወራ፤ ስለ ችግርና መፍትሄው ተመከረ፤ በመጨረሻም ለህክምና የተጠየቀችውን\n4 ሚሊዮን ሽልንግ ለመሙላት ሁሉም ያለውን እንካችሁ አለ። ግላዲ በዚህ በጎዳና ህፃኑ ጆን ምክንያት ለህክምና የሚሆናት ገንዘብ በህዝብ መዋጮ ተሟልቶ ወደ ህንድ\nተጉዛ ታክማ ኦክስጅኗን ጥላ ዛሬ በነፃነት፤ በመታገዣ ሳይሆን ተፈጥሮ በሰጣት ትተነፍሳለች፤ ትንቀሳቀሳለች። እንግዲህ እንዲህ ነው፤\nለመስጠት የግድ ሀብታም መሆን አይጠበቅብንም። ልስጥ ብሎ የተነሳም የሚሰጠው ፈፅሞ አያጣም። በጎ ሐሳብም ቢሆን ሌላን የሚያንፅ\nሌላውን የሚያቆም ነውና። እኛ መልካምነትን\nተላምደን ወደ ሌሎች ማስረፅና ለሌሎች መልካም ገጠመኝ ምክንያት እንሆን ዘንድ፤ መልካምን ነገር አቅማችን በፈቀደው መልኩ እንተግብር።\nምን አልባት አቅማችን ለመተግበር ካላበቃን፤ መልካም ነገርን ማዘዝና በበጎ ሐሳብ ጉዳዮች መግለፅ እንልመድ። ለመልካም ተግባር ማነሳሳት\nካልቻልን ቢያንስ መልካም ነገር መመኘት የምናዘወትረው ተግባር ቢሆን ዓለም ምንኛ በቀናች ነበር። ደጋግ ዘመኖች እንዲመጡ በጎዎችን\nያብዛልን አበቃሁ። ቸር ይግጠመን።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2012 ተገኝ ብሩ", "passage_id": "73bfd82cb831875166f2390a7e012ed6" }, { "passage": "አየህ አንዳንዴ ቁስል ሲደርቅ፤ ጠባሳም አብሮ ይጠፋል። ያኔ ነው የመዘንጋት አባዜ የሚሳፈር። መዘንጋት ደግሞ ‹‹pure›› በሽታ ነው። ህመምህ ሳይድን ሰንበርህ እንኳን ቢጠፋ፤ ማን እንደለጠለጠህ ካላወክ የገራፊህ ወዳጅ ሆነህ፤ ለክፍል ሁለቱ አርጩሜ ጀርባህን እያደነደንክ ትጠብቃለህ። \nእመነኝ ወዳጄ የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም ቢሆንም ቅሉ፤ አባባሉ! ትዝታ ላይ ድር ሲያደራ ያኔ… አንዳንዴ! አንዳንድ ጊዜ ብቻ…የተወጋም ይረሳል። አዳም በስንብት ቀለማት እንዲህ ይላል… ለእያንዳንዱ ሰው የት እንዳለ የሚያሳየው፤ ካርታ እየተሰራ ካልተሰጠው፤ አፉን ሚጥሚጣ ባሞቀው ቁጥር አዋቂ ሊሆንብን ነው…እናማ ወዳጄ የቆምክበትን ካርታ ጎንበስ ብለህ አስተውል። ምናልባት የመዘንጋት አባዜ ተጠናውቶህስ ቢሆን? ግን እኮ መዘንጋት ባይሆንም ሱስም ሊሆን ይችላል። የመቀጥቀጥ፣ የመሰደብ፣ የመሰደድ… አባዜ። \nእናም አንዳንዴ የወጋ ብቻ ሳይሆን የተወጋም ይረሳል። ‹‹መቼ መቼ?›› ካልክ መልሱ ይሄውልህ…. ጠባሳህ ጠፍቶ ትውስታህ በጭጋግ ሲጋረድ፤ የታሪክ ሚዛኑ ተዛብቶ የቆመበት መሬት ሲክድህ…ማስተዋል እርቆህ ከጠላትህ ጋር ትጣባለህ። ቁስልህ ሽሮ ያልተነካህ ቢመስልህ፤ ያን ጊዜ ነው…የተወጋ የሚረሳ። \n‹‹ፍትህ ትወዳለህ ፍትህ እንደጎደለ እያወክ ግን ዝም ትላለህ። አየህ ይሄ አንድ ሰው ሲከፋፈል ነው›› ይልሃል አዳም፤ ጎጥ የሸበበው ሽል ውስጥ ተሸሽገህ መላ ቅጡ ጠፍቶህ ሲያይህ። ቆሜለታለው የምትለው ቀድሞ ሲሞትልህ፤ ፍሬው ሳይደርስ ተስገብግበህ አጨድከው። እናም የቆምክበትን ካርታ ተመልከተው፤ በሳር ውስጥ ካለ እባብ ጋር ወዳጅ መስሎህ ለምደህ ይሆን? \nምን መሰለህ ወንድም ዓለም ምላስም እኮ ያዳልጣል። አንዳንዴ ህሊናም ከራስ ይሸሻል። ታዲያ ሰንበርህ ከውስጥ ተሸፍኖ የጠፋ መስሎ ቢያስትህ፤ ከምኔው ከጠላቶችህ ተወዳጅተህ አዛኞችህን መንከስህ። ሙሾ አውራጅ እንዲህ ትላለች፤ የደረቀውን የእንባ ቀረጢቷን በአይበሉባዋ እያሸች…‹‹ወይ እኛና ዶሮ፤ አሞራና ሞት ሲመጣ መንጫጫት፤ ሲሄድም መርሳት››…ዛዲያማ ወንድሜ ከገባህበት ማቅ ለመውጣት የህሊናህን ድር ጠራርጋት። የማስተዋልህን በር ክፈታት… \n‹‹አህያውን ፈርቶ ዳውላውን›› እንዲሉ… በከሰረ፣ በተንሸዋረረ የጥላቻ ‹‹ቦጠሊቃ›› አውቀህ ያስተኛህው ህሊናህ አንተን ብቻ ሳይሆን ያመነህንም ገደል ሊከት ነው። ‹‹በእንኪያ ሰላምታ›› እውነትህን አርቀህ ቀብረህ ‹‹ስተህ ለማሳት›› ልብህን ምን አበረታው? \nአየህ የተወጋ ሲረሳ… ለተዛባ ፍትህ ቆሜያለሁ ብሎ፤ ንጋትን ለማጨለም ይጣደፋል። ያመነበት ሲሳካ፤ ጉም የዘገነ ይመስለዋል። ትናንቱ እንደ ገደል ማሚቱ ጮሆ ይጠራዋል። ሳይጠጣ እንደሰከረ፣ አሁንም አሁንም እንደሚወላገድ፤ የቆመበት መሬት ስምጥ ገደል እንደሆነ ይታየዋል። ታሪክን ያጨልማል፤ በጭካኔ ተሞልቶ ምስኪን ገበሬን ይከሳል። የእርሱ ያልሆነን ያማትራል…ከአራጁ እየዋለ የበቀለ…በትን መሬት ይክዳል። ለካ የተወጋም ይረሳል….።ከገዳዩ ጋራ አብሮ መሬት ይምሳል። \nአዲስ ዘመን ግንቦት 9/2012\nዳግም ከበደ", "passage_id": "203f9ed28e539b2c365fe517812e41eb" }, { "passage": "የሩቅ ጊዜ እውነተኛ ታሪክ ነው።ምን ለብሼ ልሳቅ የሰውየው እውነተኛ ስሙ አይደለም።በነገር አገደም አግራሞት የሚያጭርበት ጉዳይ ሲያገኝ ከት ብሎ እየሳቀ ምን ለብሼ ልሳቅ ስለሚል ነበር አካባቢው መንደርተኛው በሩቅ የሚያውቁትም ጭምር በዚህ ስያሜ የሚጠሩት።መለያው መጠሪያ ስም ሆኖ ጸደቀለት። አዳሩ\nበዚያን ዘመን ይሰሩ ለነበሩ ቤቶች ከአሰሪዎቹ ከባለቤቶቹ ጋር ተዋውሎ ጭቃውን በጭድ እያቦካ በደንብ በተለያየ ቀናት አገላብጦ ፈርመንትድ ሲሆን (ሲበስል) እንበለው የተማገረውን አዲስ ቤት ደህና አድርጎ በጭቃ ይመርገዋል።በኋላም የልስን ስራ ይሰራል።የእኛ ሀገር የቀደመው ዘመን ሲሚንቶአችን መሆኑ ነው።ዛሬም በስፋት ይሰራበታል፡፡ ብዙዎቹ የሀገራችን ቤቶች\nየሕዝቡ የመሳፍንቱና መኳንንቱ ሳይቀር ምሰሶው ቆሞ ወጋግራው ከተዋቀረና ከተገደገደ በኋላ የሣር ክዳን ይደረግለታል።ዙሪያውን የሚለሰነው ምርጥ ብቃት በነበራቸው የሀገራችን ጭቃ አቡኪና ለሳኞች ነው።ስንቱን ከተማ መንደር ሰፈር አብረው እንደቆረቆሩ፤ ስንቱን ቤት እንደሰሩ፤ የሚናገርላቸው የሚጽፍላቸው ጠፍቶ እንጂ ሰዎቹስ ምርጥ ባለሙያዎችና ባለታሪክም ነበሩ። እነ ምን ለብሼ ልሳቅን የመሰሉ ብዙ ሺዎች ፡፡ ምን\nለብሼ ልሳቅን ለየት የሚያደርገው ለየት ያለ ባህርይና አስገራሚም ስለነበረ ይመስለኛል። ግጥም የለውም። መንደርተኛና ሰፈሩ በአለባበሱ ይደመማል። ትልቁም ትንሹም።ሲመጣ ሕጻናት ይከቡታል። ያውካካሉ።ሱሪ 2 ኮት 3 ሸሚዝ 2 ከረባት 4 ሁልጊዜም መነጽሩ ባዶና መስታወት የሌለው፤ በሸሚዞቹ ኪሶች ላይ የሚሰሩና የማይሰሩ ብዙ እስክሪቢቶዎች የሚደረድር ሰው። ጸጉሩ በዘመኑ ፋሽን ኤልቪስ።ዘመኑም የእነ ኤልቪስ የዝነጣ ዘመን ነበር። በጫማ ላይ ጫማ ስለማይደረግ እንጂ እሱንም ለማድረግ አይመለስም ነበር። በዚያን ዘመን\nእንዲያ ለብሶ ከገጠር መንደር ብዙም በማትለየው የአዲስ አበባ ጥርጊያ መንገዶች ላይ ሽር ብትን እያለ በቄንጥ ሲራመድ የሁሉንም ቀልብ ይስባል።‹‹ኧረ ሳቄ መጣ›› ያሠኛል።እሱ ማንንም ከቁብ አይቆጥርም። ይህ ሰው ማነው ለሚለው ማንም መልስ አላገኘለትም።ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ ወይንም ለመጠላት ወይ ለመወደድ እንዲሉ ሆነና። አዕምሮው ልክ\nአይደለም ባዮች ብዙ ነበሩ።እነሱ እንጂ እሱማ ልክ ነኝ ብሎ ነው የሚኖረው፤ የሚሰራው።የተዋዋለውን ስራ ጭቃ ማቡካቱንና መለሰኑን አሳምሮ ይሰራል።ስራ ሲሰራ ይዘፍናል።ሰው ሰማ አልሰማ ደንታ የለውም።ዘፈኑ ሁሌም ‹‹አንቺ ልጅ›› ነው። ‹‹አሀሀሀ አንቺ ልጅ፡፡›› ምናልባት ምናልባት ይሄ ስለሚሰራው ስራ እንጂ ስለማንነቱ ብዙ የምይታወቀው ሰው ከጀርባው ምን ታሪክ ተሸክሞ ይሆን የሚለው ጥያቄ የብዙዎች ነበር። የት ተወለደ፤ አደገ፤ ተማረ፤ ቤተሰቡስ የት ነበር? ምንም ፍንጭ የለም።ብዙ ሰዎች ለማወቅ ጥረዋል።ሲጠይቁት መልሱ አጭር ነው ምን ለብሼ ልሳቅ ይልና ይንከተከታል።ምናልባት በሰዎቹ በመገረም አሊያም ዓለምን በመናቅ ሊሆን ይችላል።እኛ ያላየነው የማናውቀው የለም በሚል ውስጣዊ ምፀት ይሆናል ከት ብሎ የሚስቀው። አዛውንቶቹ ወጣቱ ሁሉም ሰው ያውቀዋል። አብዝተው ይገረሙበታል። በማይታወቀው ማንነቱ። በዚህ ሰው ማንነት ውስጥ ሌላ የተሰወረ የተደበቀ ማንነት አለ።ግን ለምን እንዲያ ሆነ ቢባል የመልሱ ባለቤት እሱና እሱ ብቻ ነው። ብዙ ሰዎች ደሞ ‹‹ምን ለብሼ ልሳቅ ይላል እንዴ፤ ይሄን ሁሉ የሀገር ልብስ ደራርቦ እየለበሰ›› ይሉና ይሽኮመኮማሉ። የሚገርመው የስራ ልብስ አለው።ለብሶ የሚመጣው ንጹህ ልብሶች ናቸው። ስራውን ሲጨርስ ተጣጥቦ ሲያበቃ ያንኑ ደራርቦ ይለብስና ሽክ ይላል። ‹‹አሀሀሀሀሀሀ አይ ምን ለብሼ ልሳቅ።›› ዛሬ ከስንትና ስንት ዓመታት በኋላ ታወሰኝ በል፡፡ ‹‹በጤናው አይደለም›› ቢሉም ‹‹እኔ እብድ አይደለሁም፤ እናንተ ናችሁ እብድ›› ይላል።‹‹ጤነኛ ነኝ›› የሚል ስንት እብድ እንዳለ መንፈሱ ሹክ የሚለው ይመስላል።ልብሱ፤ ከረባቱ፤ ሸሚዙ ኮቶቹ ይቀያየራሉ።ወይ ሰዎች ይሰጡታል ወይ የራሱ የሆነ የተከማቸ አለው።ለስራ ተዋውሎ ሲመጣ እንጂ መኖሪያው አይታወቅም የምን ለብሼ ልሳቅ።እንደሌሎቹ የእሱን አይነት ስራ እንደሚሰሩት ሰዎች ጠላ፤ ጠጅ፤ አረቄ፤ ቤት አይታይም።ቢሰጡትም አይጠጣም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን እንደዛው ለብሶ አልፎ አልፎ ግሮሰሪ እንደሚገባ በሥርዓቱ ቁጭ ብሎ አዞ የተወሰነ አልኮል እንደሚጠጣ ይናገራሉ።አንድ ጊዜ ቁምጣ ሱሪውን አድርጎ በባዶ እግሩ ጭቃውን ሲለውስ ከቤታቸው ውሀ ልክ ላይ ቁጭ ብለው ሁለት የተማሩ ወጣቶች ምስጢራቸውን በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያወራሉ። ማንም ሰው አይሰማንም ነው ነገሩ።መቼም ምንም ቢያስቡ ሊጠረጥሩ አይችሉም። እሱ ስራውን ይሰራል። ሰማ፤ ሰማ ፤ሰማና መጨረሻ ስራውን ከውኖ ተጣጥቦ ሲያበቃ ያንኑ አስገራሚ ልብሱን ከረባቱን ባዶ መነጽሩን አድርጎ ለማረፍ በሚመስል መልኩ ተማሪዎቹ አጠገብ ቁጭ አለ።እየሳቁ ምን ለብሼ ልሳቅ ታዲያስ አሉት።በተለመደው ሳቁ አውካካ።አይ እናንተ አሁን ምስጢራችሁ እንዳይሰማ ነው አይደል በወፍ ቋንቋ የምታወሩት አላቸው።‹‹ልክ ነህ ማንም እንደማይሰማ እርግጠኞች ነን›› አሉት።የተነጋገሩት ስለአብዮትና ለውጥ ስለንጉሱና ሥርዓታቸው የእኛስ በምን መልኩ ነው መሄድ ያለበት የሚል ነበር፡፡ የወጣቶቹን አፍ ያዘጋ ድንጋጤ ውስጥ የከተተ ድንገተኛ ምትሀት የመሰለ ጉዳይ ተከሰተ።በጠራ እንግሊዝኛ የተወያዩበትን ዘርዝሮ ጥያቄአቸውን በመለሰ መልኩ ነገራቸው ጭቃ አቡኪውና ለሳኙ ምን ለብሼ ልሳቅ።ደነገጡ።ማመን ተሳናቸው።እሱ ነው ሌላ ሰው እስኪሉ ድረስ።መጽሐፍቶችን በስም እየጠራ ይሄን ይሄን አንብቡ ሲላቸው ድንጋጤአቸው ሽቅብ ጎነ።ግን አላቸው ለማንም አትናገሩ ቃል ግቡልኝ። እኔ በዚህ መልኩ የምሰራው የምኖረው የእራሴን ኑሮ ነው።ደስተኛ ነኝ።ዓለምን ንቄ ሰውንም እርቄ ነው ብሎ በረዥሙ ተነፈሰ። እንዴት ብዙ የተማረ ሰው በሌለበት ሀገር የዚህ እውቀት ባለቤት አንዱ ጋ ተቀጥሮ መኖር\nሲችል ይሄንን አይነት ኑሮ ለመኖር መረጠ በሚል ወጣቶቹ በእጅጉ አዘኑ።ተደናገጡ።እሱ ግን አላቸው።ለእኔ አታስቡ አትጨነቁም።በጉልበቴ ሰርቼ እኖራለሁ።ስራ አከብራለሁ።የሰው እጅ አላይም።ልመና አልወድም።ዓለምን ስትረሳት ትረሳሀለች። ሁሉን ከረሳህ በትላንት ውስጥ ካልቆዘምክ ትኖራለህ በሉ ቻው አለና ተነስቶ ግቢውን ጥሎ ወጣ።ጉድ ጉድ ሲሉ ውለው አደሩ።ምን ለብሼ ልሳቅ ማነው።ከአሁኑ ትንሽ መገለጥ በቀር ስለዚህ ሰው ማንም ምንም አያውቅም። ሌላ ሰፈር ሄዶ ያንኑ ጭቃ ማቡካት ሲሰራ እንዲሁ የ11ኛ\nክፍል ተማሪዎች በራፋቸው ላይ ቁጭ ብለው በተሰጣቸው የታሪክ ትምህርት የቤት ስራ ላይ በእንግሊዝኛ እያወሩ ይከራከራሉ።የያኔ ተማሪ ብርቱና የቀለም ቀንድ ነበር።ለወረቀት ሳይሆን ለእውቀት የሚተጋ።ለእውቀት የሚታትር ንብ።አንባቢ፤ተከራካሪ፤ሞጋች።ብርቱ የቀለም ደቀመዝሙርና ካህን።መምህሮቹም በእውቀት የላቁ የረበቡ።እሱ ጭቃውን ጭድ እየነሰነሰ ይለውሳል።ተማሪዎቹ በጥያቄው መልስ ላይ አልተስማሙም።ተነታረኩ።አጠገባቸው ወትሮም የሚያውቁት የሚስቁበት ምን ለብሼ ልሳቅ ብቻ ነበር።ሌላ ሰው የለም። አከራካሪው ጥያቄ በፈረንሳይ አብዮት ላይ ያተኮረ ነው።ምን ለብሼ ልሳቅ አካፋውን ይዞ ጭቃውን እያገላበጠ ይሰማቸዋል። አላስቻለውም። ዝምታውን በድንገት ሰበረና ከት ብሎ ሳቀ።አንዱ ተማሪ ይሄ እብድ ምን ይስቃል ሲል አዎን እብድ ነኝ። ዘመን ያሳበደኝ በራሴ ዓለም የምኖር እብድ አለው። መልሱ ልጁን አስደነገጠው። ምን ለብሼ ልሳቅ ለጠቅ አደረገና በጠራ እንግሊዝኛ ምንድነው የምትጨቃጨቁት ሲላቸው በተቀመጡበት ክው ብለው ቀሩ። እሱ ነው የተናገረው ሌላ ሰው በሚል ጥርጣሬ።ደገመላቸው። የተከራከሩበትን ነጥብ በነጥብ እያነሳ ከመነሻው እስከ መድረሻው አካፋውን ይዞ ቆም እንዳለ አነበነበላቸው።መልሱ ይሄ ነው አለና በረዥሙ ተነፈሰ፡፡ ተማሪዎቹ አብዝተው ተደመሙ።ግን አላቸው ስለእኔ ለማንም አታውሩ ።ስለእኔም አትጨነቁ።አትመራመሩ።እኔ በራሴ የሕይወት መንገድ ደስተኛ ነኝ። ከማንም ምንም እርዳታ አልፈልግም። እስካለሁ በጉልበቴ ሰርቼ እኖራለሁ። ስራዬን አከብራለሁ።እናንተ ግን በርትታችሁ ተማሩ።አንብቡ። ለወረቀት ሳይሆን ለእውቀት ትጉ አላቸው። በተቀመጡበት በድንጋጤ ተመቱ። ከጭቃው ውስጥ ወጥቶ ተጣጥቦ ልብሱን በተለመደው ሁኔታ ለባብሶ ቻው ብሎአቸው መንገዱን ቀጠለ። ግዜው የ1966 አብዮት ዋዜማ\nነበር።ምን ለብሼ ልሳቅ ማነው? እውነተኛ ስሙና ታሪኩስ? ምን ገጥሞት ምንስ ሆኖ ይሄን የሕይወት መንገድ መረጠ? አዲስ ዘመን ሀምሌ 18/2011", "passage_id": "304fd91821603631b9bad2d841cc81b3" }, { "passage": "በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ ማግባት፣ መውለድና መሞት የማይቀሩ ወሳኝ ኩነቶች ተብለው ቢቆጠሩም ማግባት ግን የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡ (አለማግባትም ይቻላል) በማህበረሰቡ ውስጥ (በተለይ ደግሞ ማህበረሰባዊ ባህልን በሚከተሉ ማህበረሰቦች) ያገቡ ሰዎች፣ ካላገቡት ይልቅ የኃላፊነት ስሜት አላቸው የሚል እምነት በመኖሩ ነው አብዛኛውን ጊዜ ጋብቻን የሚመርጡት (መውለድና መዋለዱ ዘርን መተካቱ ‹‹ሌላውም›› እንዳለ ሆኖ) በማህበራዊ ግንኙነት ውስጥ የሚገኘውን ደረጃ መጨመር የማግባት ማህበራዊ ጥቅም ነው ልንለው እንችላለን፡፡\nወገን ጉዳዬ ጋብቻን ማስረዳት ሳይሆን ተያያዥ መዘዙን ለመግለጥ ነው፡፡ (በቃ ወቅቱ የሰርግ ስለሆነ አግብተህ መሆን አለበት እያላችሁኝ ይሆን?) አትሸወዱ እኔ እንኳን ግራ ጎኔን በመፈለግ ሥራ እየተጠመድኩ ነው፡፡ አፈቅርሻለሁ እንጂ አፈርጥሻለሁ ሳልል ሴቶች ሁሉ ሲያዩኝ ስለሚሸሹኝ እስካሁን ማግባት አልቻልኩም፡፡አንድ ጊዜ ስጠራት 99 ጊዜ አቤት የምትለኝን ሚስት ለማግኘት ግን ፈጣሪን ተማጽኖ ላይ ነኝ፡፡ (ታዲያ ለምን ትተረተራለህ አትሉኝም) አትሉም እኮ አይባልም ግድ የለም በሉኝ፡፡ መቼም በአገሬው ብሂል ‹‹ነገርን ከሥሩ ውሃውን ከጥሩ›› ይባል የለ ተንደርድሬ ‹‹ወደ ገደለው›› ከምገባ ላዩን አሳይቼ ስለምን ለማውጋት እንደፈለግኩ በጽሁፍ መግቢያ አንቀጽ ፍጆታዬን ማሳያ ነው፡፡ ከጋብቻ ይልቅ በጋብቻ ምክንያት የሚወጣው የድግስ ወጪን የሀሳቤ ማጠንጠኛ ለማድረግ እንዳሰብኩ ተገንዘቡልኝና አብረን እንዝለቅ፡፡መቼም በከተሞች የሚደረጉ ጋብቻዎችን በአንክሮ የተመለከተ ሰው ከእኔ በላይ ትዝብት እንደሚኖረው አልጠራጠርም፡፡ በተለያዩ ህብረ ቀለማት አበቦች ያሸበረቁ የሠርገኞች መኪኖች በየመንገዱ የጋብቻ ማስታወቂያ ጩኸት እያሰሙ ቪዲዮ እየተቀረጹ አደባባዮችን ይዞራሉ፡፡ ባለ ሁለት ጎማ (እግረኞች) የሆንን ደግሞ ይህንን የሠርግ ትዕይንት ያለ ክፍያ መመልከት ልማዳችን ነው፡፡ ብዙ ሠርገኞች ከአደባባዩ ቄንጥ በላይ ለሠርጉ የሚያወጡት ወጪ ያናድደኛል፡፡ በተለይ ለአንድ ቀን ታይታ ብለው ዕድሜ ልካቸውን ብድር ሲከፍሉ የሚኖሩ ሰዎች፡፡ከማን አንሼ የምትለው ኢትዮጵያዊ መፈክራችን ስንቱን ሰው አፈር ድሜ አስበልታዋለች መሰላችሁ፡፡ የዛሬ ሁለት ዓመት ቅልጥ ያለ ሠርግ ደግሶ ያገባው የመንደሬ ሰው ‹‹የዕዳ ድሩ›› እስካሁን አልተ በጣጠሰም፡፡ አሁን አሁን የጠዋት ጸሎቱ ቀኝ አውለኝ ሳይሆን ‹‹እባክህ ሸረሪቷን ግደልልኝ!›› ሆኗል፡፡ ሚስጥሩም ዕዳዬን አቅልልኝ ከማለት አበዳሪዬን የሰማይ ቤት ቪዛ ስጥልኝ እንደ ማለት ነው፡፡ይህ ያልሞላለት ልታይ ባይ ከአቅም በላይ ደጋሽ በሁለት ዓመት የትዳር ኑሮው ትዝታው ውስጥ የቀረው የግድግዳው ፎቶ ብቻ ነው፡፡ የዛኔ አብረውት ሠርጉን ያደመቁ የበሉና የጠጡ ሰዎች የአንድ ቀን አድናቆት ሰጥተውታል እንጂ የቤቱን ጎዶሎና ገበና መች አዩለት፡፡ እርሱ ግን ከዚህ ሁሉ ምጥ መገላገል አቅም አጥቶ በቀን አምስት ጊዜ ከንፈሩን እየነከሰ ይገኛል፡፡ አጋጣሚውን አግኝታችሁ ይህንን ሰው ‹‹እንዴት ነው ኑሮ?››ብትሉት ‹‹ተመስገን ነው የሞላልኝ የስልኬ ባትሪ ብቻ ነው›› ማለቱ አይቀርም፡፡ ታዲያ እርሱንና መሰሎቹን ያየ ሰው ሠርግ መደገስ ያምረው ይሆን? (ልጥጦችን አይመለከትም)ያለውማ ከአንድ በላይ ቢደግስስ ምንችግር አለው፡፡ (ታዲያ ሌላ ሚስት ያግባ ማለቴ አይደለም) በነገራችን ላይ አዲስ አበባ ላይ ብዙ የሚወራለት አንድ ቅንጡ ባለ ሀብት አራት ጊዜ እኔ ነኝ ያለ ሠርግ ደግሶ ብዙ ሀብታሞችን በወይን ማራጨቱን ታውቁ ይሆን? እንግዲህ ሰርጉን ይሁን ሚስት መቀያየሩን የወደደው ባይታወቅም አራት ጊዜ ጋብቻ ማከናወኑ ቅንጣት እንዳላጎደለበት እንኳን አሁንም ለማግባት ሽር ጉድ እያለ መሆኑን ሰምቻለሁ፡፡ የሚገርመው ለአራተኛ ጊዜ ያገባትን ሴት ‹‹ባንቺይርጋ›› የሚል የዳቦ ስም አውጥቶላት ነበር መባሉንም ሰምቻለሁ፡፡ ልማድ ነውና ቀጣይ የማግባት ዓላማ ካለው ደግሞ አምስተኛዋን የመጀመሪያዬ ይላት ይሆናል ማን ያውቃል፡፡እንደኔ ዓይነቱ ኪሱ ከሲታ የሆነ ሰው ደግሞ እነዚህን ሰዎች እያየ ነው እኩል ካልሆንን እያለ ለመደገስ የሚሯሯጠው፡፡ የማይመጥነንን ህይወት በማየት አጓጉል ቅናት ማሳደር ተገቢ አይመስለኝም፡፡ በብዙ ርቀት ላይ ያሉ ሰዎችን ኑሮ ማየትና ከኛ ህይወት ጋር ማነጻጸሩ መጨረሻ ላይ የራሳችንን ኑሮ እንድንጠላ ያደርጋል፡፡ወዳጄ ከሌለህ የለህም ነው፡፡ ዛሬ ከአቅም በላይ ደግሰህ ያበላኸው ሰው ነገ ዞር ብሎ አያይህም፡፡ ከአቅም በላይ መንጠራራት ትርፉ ለመውደቅ ነው፡፡ በዚህ ዘመን አትውደቅ ‹‹ከወደቅክ ይህ ህዝብ የሚያነሳህ በካሜራ ብቻ ነው›› የሚለው ተረት እንዳይደርስብህ ደግሰህ ግራ ከምትጋባ ተግባብተህ ግባ!ጥር 24/2011አዲሱ ገረመው", "passage_id": "38f70726106e91b4f95e6017c4330d68" } ]
752595b3b465c2774ad5485baddb731b
719b94f542105ed071d70ab0e6fcd2a1
የበዓል ሰሞን ስብሰባዎች!
አበባ አየሁ ወይ፤ ለምለም… አበባ አየሁ ወይ ለምለም….ባልንጀሮቼ፤ ለምለም ግቡ በተራ …” ጠዋት ቀድሜ የሰማሁት የአዲስ ዓመት መዳረሻ ብስራት መንገሪያ የልጃገረዶች ጨዋታ ነው ። እርግጥ የዘመኑን ያህል በለውጤ ላይ ባላምን ደስ ብሎኛል። አዲስ ዓመት እንደኛ የሚደምቅለት ወይም የሚደምቅበት አለ? ግን አይመስለኝም፤ ተፈጥሮ ሁላ አበባ አፍክታ፤ የሰማዩ ደመና ሁሉ ተገፍፎ፤ ብርሃኑ ሲገልጥ አዲስነት በተፈጥሮም ላይ ሲነግስ እኮ ነው ዘመናችንን የምንለውጠው፡፡ ይህ ከተፈጥሮ ጋር በጋራ የምንለውጠው አዲስነት አያስደስትም? በጣም እንጂ! “አዲስን ዘመን በአዲስ መንፈስ መጀመር ጥሩ ነው፤” ሲሉ ደጋግሜ ሰምቻለሁ ። ደስ ሲል! ያ ለውጥም በአዲስነት ላይ መገኘት ትልቅ ነው ። አዲስነት ተሰማኝ! ለዚያውም በማለዳ ስንት መርዶ በሚነገርበት ሀገር ላይ የአዲስ ዓመት ብስራት፤ አዲስ ዘመን ነጋ ዜማ መስማት መታደል አይደል? አዲስ አበባ የበዓል ሰሞን ሩጫዋ ሰርገኛ ጠርታ ደጅ ላይ ያስቆመች፤ የምታበላው ያለሰናዳች ሙሽራ ያስመስላታል ። የበዓል ሰሞንማ ባልዋን ለመጀመሪያ ጊዜ ያየች ሙሽራ ያህል ጭንቀቷ ይበረታል ። የበዓል ድባቡ ከትርምስ ጋር የተደበላለቀ ሁነት፤ ደስም ጭንቅም ያሰኛል ። አውዳመት የኛን ያህል የሚደምቅለት አለ ግን? በዓሉን ለማክበር የምናሰናዳው ነገር መብዛቱ የምነከውነው ተግባር ማየሉ አንድ ቀን ብቻ አክብረነው የሚያልፍ እኮ አይመስለም ። እኔ ምለው? ይሄ ሁሉ የበዛ ክብረ ባዓላችን ድምቅምቅ አድርገን እያከበርን ምግብ በየአይነቱ፤ የሚጠጣ በየወንጪቱ፤ አቅርበን እየላፍን…፤ እያሻመድን የኑሮ መወደድ ሳያነቃንቀን፤ የጊዜ መቀየር ሳይለውጠን፤ የቀጠልነው በምን ይሆን? ኑሮ ተወደደ፤ ረከሰ፤ ተሰቀለ፤ ተዘፈዘፈ፤ ዓመት በዓል ዓመት በዓል ነው። ሁላችንም ዘንድ ከየትም ተጠረቃቅሞ ቤት ይሞላል ። በእኩልነት ሁሉም በጋራ ይስቃል፤ በአብሮነት ጨዋታው ይደራል ። እንደምናከብራቸው በዓላት ብዛት፤ እንደምንደግሰው ድግስ ስፋት አዘውትረን ችግር የምናወራ፤ ድሎት የራቀን አንመስልም እኮ! ውዶቼ፤ ትናንት ቤታችሁን የዋላችሁበትን አስቡት እስኪ? ከኑሮና አኗኗራችን በላቀ፤ ከምግብና አመጋገባችን በተለየ የአውዳመት ድግሳችን የተለየ ነው ። እንዲያው በበረከቱ ቤታችንን እየሞላው እንጂ ተማርረን የምንገልፀው አጥተን ነጣን የበዓል ቀን ላይ በልተን ወዛን ይለወጣል ። ሰው ግን ከየት ነው ይሄን ብር የሚመጣው፤ አውዳመት እየጠበቀ የሚረጨው? የሆነ ያልታወቀማ ምንጭ አለ ። ግድ የላችሁም ውዶቼ፤ ሰዎች ከገቢያቸው በላይ ሲያወጡ ካላቸው በላይ ሲነጩ መጠርጠር ጥሩ ነው ። በዓመት በዓል ላይ የሚፈልቅ፤ አውዳመት ላይ የሚፍለቀለቅ አንድ ያለታወቀማ ምንጭ አለ መሰለኝ ። የሰዎች ብር ማግኛ መንገድ የተለያየ፤ የገቢ ምንጫቸው ለየቅል ቢሆንም ሰሞኑን በአንድ አጋጣሚ ከስራ ባልደረባዬ የሰማሁት የበዓል ሰሞን ስብሰባዎች ገጠመኝ ግን ገርሞኛል ። በዓላት በደረሱ ጊዜ የስብሰባዎችን መብዛት ዋነኛ ምክንያት እንዳጤነው አደረገኝ። እኔ ምለው በዓውዳመት ሰሞን ስብሰባ የሚበዛው ለምን እንደሆነ ጠይቃችሁ ታውቃላችሁ? ጉዳዩ ወዲህ ነው ወገኖች፤ ግርግሩን ተጠቅሞ ኪስ ለመሙላት፤ በዓልን አስታኮ ትርፍ ለመብላት ነው። የበዓልን ግርግርና አውዳመት በመጣ ቁጥር የሚዘጋጁ ስብሰባዎች የዛሬው ትዝብት ማጠንጠኛዬ ሆኗል ። የዓውዳመት ሰሞን፤ በተለይ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በስብሰባ ይጨናነቃሉ ። በዓል ሲቃረብ ስልጠና መስጠት፤ ሰበብ ፈጥሮ መሰባሰብ ተለምዷል። ሰብሳቢውም ተሰብሳቢውም በስብሰባው አላማ ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ ከስብሰባው የሚገኘው ብር ወይም አበል ላይ ያተኩራሉ ። በአንድ ጊዜ ሁለት ስብሰባዎች ላይ በመገኘት ከሁለቱም ቱርፋት ለመቋደስ የማይወጡት ዳገት የማይወርዱት ቁልቁለት የለም። ለወጌ መነሻ የሆነኝ ባልደረባዬ በስራ አጋጣሚ በታደመባቸው ስብሰባዎች የገጠመውን ሲነግረኝ፤ የታዘበውን ሲያወጋኝ የተገረምኩበት ጉዳይ ለዚህ ጽሁፌ መነሻ መሆኑን ነግሬያችሁ የለ ። አግራሞቴ እንዲጋባባችሁ የራሴን ገጠመኝ አክዬ ገጠመኙን ላውጋችሁማ ። ስበሰባ የሚበዛበት የበዓል ሰሞን ላይ የተከሰተ ነው ጉዳዩ፤ ለበዓል መዋያ ይሆን ዘንድ አበል ተበጅቶ መርሀ ግብር ተነድፎ የሁለት ቀን ስብሰባ አራት ወይም አምስት ቀን ተብሎ የሚከፈልበት ሰሞን፤ አውዳመትን ለመውጣት የሚያስችል ገቢ ማግኛ ይሆን ዘንድ የታሰበ ስብሰባ፤ ከአዲስ አበባ ወጣ ብሎ በሚገኝ መስሪያ ቤቶች በክፍለ ሀገር አበል ለመክፈል ሲያስቡ ስብሰባ አብዝተው የሚያደርጉበት ከተማ ላይ ነው የባልደረባዬ ትዝብት መነሻ ቦታው፤ አንድ ተሰብሳቢ በሁኔታው የባልደረባዬን ትኩረት ይስብና ባልደረባዬ ሰውዬውን መከታተል ይጀምራል። ሰውዬው በተደጋጋሚ ከስብሰባው ወጥቶ ይገባል፤ በመሀል እየጠፋ አመሻሽ ላይ ይመጣል ። ይሄን የተመለከተው ወዳጄ “የት እየቆየህ ነው ምትመጣው?” ብሎ በገደምዳሜ ይጠይቀዋል ። ያ ወጥቶ ይገባ የነበረው፤ ጠፍቶ አምሽቶ ይከሰት የነበረው ሰው ምላሹ አስገራሚ ነበር ። ሌላ ቦታም ስብሰባ እየተካፈለ መሆኑንና በአንዴ ሁለት ስብሰባ ላይ እየታደመ መሆኑ አበል ሁለቱም ቦታ እንዳያመልጠው ለፊርማ እየተመላለሰ መሆኑን ነገረው ። ጉዳዩ አግራሞትን አጭሮበት ነበርና ከትውስታ ማህደሩ በጫወታችን መሀል አካፈለኝ ። የሰውዬው ሁሉ አይቅርብኝ ባይነት አያስገርምም? ባልደረባዬ የስብሰባ ገጠመኙ ሌላ ተመሳሳይ ሁለት ስበሰባ ተካፋይ ሰው ጋርም አገናኝቶት አልፏል። ይሄኛው ሰውዬ ግን አትራፊ ሳይሆን አጉዳይም ነበር ። ከአንደኛው ስብሰባ ወደሌላው እየተመላለሰ የትራንስፖርት ወጪ እያወጣ ለቀናት ሁለቱም ቦታ ‘አለው’ ሲል ከርሞ ስብሰባው አበል አልባ መሆኑ ተነግሮት አተርፍ ባይ አጉዳይ አድርጎታል። ሃላፊዎችስ ቢሆኑ የተቋማቸውን አደራ፤ የህዝብን ተልዕኮ ለመፈፀም ተቀምጠው የዓመት በዓል ኪስ መሙያ፤ የአውዳመት ወጪ መሸፈኛ የሚሆን አበል መፍቀዳቸው ለምን ይሆን? ይህቺ ሀገር ሌላ አሳቢ፤ ሌላ ተቆርቋሪ ያላት ይመስል ክፍተቷን መሙያ ደጅ ደጁን እያየች ከኪስዋ የምናጎድለው ለምንድን ነው? እንደ ዜጋ እንቆርቆር! የራሳችንን ለመሙላት ስንሮጥ ከሀገር ላይ ማጉደላችን ምን የሚሉት በደል ነው? አዲስ ዘመን ጀምረናል ። እኛ አዲስ ባንሆን እንኳን በተዘጋጀልን አዲስነት ውስጥ የምናልፍ፤ ባናቅድ እንኳን ለአዲሱ ዘመን በታቀደ የምንምቧች፤ ንቁዎች መሆን ግድ ይለናል ። ለሀገር ማሰብ፤ ለወገን መቆርቆር የተጣለብንን አደራ ለመወጣት የምንጥር አዲስ ሰው መሆን ያሻናል ። ተገቢ ያልሆነ አሮጌነትን ከውስጣችን አውጥተን የሚገባንን መልካምነት ወደኛ ማስረጫ አዲስ ጅማሮ፤ አዲስ ሀሳብ፤ አዲስ ዘመን! ውዶቼ፤ አዲስ ለመሆን ተዘጋጅታችሁ፤ አዳዲስ ውጥን ወጥናችሁ በአዲስ መንፈስ አዲሱን ዓመት ከጀመርን ይሄው ሁለተኛ ቀን ላይ ተገኝተናል ። አዲሱ ዓመት ለማንም አይገባም ለኛ ማድረግ በአዲስነቱ የምንታደስበት ሊሆን ይገባል ። ዘመኑን የኛ ለማድረግ ዘመኑ ላይ የሚመጥን መልካም ነገር ማቅረብ ተገቢ ነው ። በነገራችን ላይ፤ የዘመኑ ሳይሆን የኛ መቀየር የኛ መለወጥ ነው ለሀገርም ለኛም የሚጠቅመው ። ወቅቱማ ዑደት ነው። ዝነፍ ሳይል የሚለዋወጥ፤ በሁሉም ስብዕናቸው ውስጥ ለውጥ ሳይኖርም የሚሄድ የሚያልፍ ። የኛ ለውጥ ነው ወሳኝ፤ በውስጣችን የምንፈጥረው፤ በልካችን የምንሰፋው አዲስ ልብስ አዲስ የሆነ መልካም ነገርን የሚያለብሰን፤ በታደሰው ዘመን እኛ አሮጌ ሆነን ከተገኘን አዲስነታችን ግን ምኑ ላይ ነው? አዲስ መሆናችን ግን የቱ ጋር ነው? ዘመኑ ሲቀየር የኛን ለውጥ በዘመኑ ካልተለካ፤ ጊዜው ሲለወጥ የኛን ለውጥ ካላሳየ የወቅት መቀያየር የጊዜ መለዋወጥ ምንም እኮ ነው ። የዘመኑ በጎዎች፤ የወቅቱ ጀግኖች፤ የጊዜው ሰላማዊ ተጓዦች ሆነን ያረጀውን ሃሳብ ወዲያ ጥለን አዲስ ዘመንን የሚመጥን አዲስነት ተላብሰን እንጀምረው፤ ዛሬ ላይ የተገኘን የዘመኑ መታደስም ሆነ ማርጀት ምክንያት እኛው ነንና ነገ በሚታየው የታሪክ ማህደር ውስጥ ዘመን አዳሾች ሆነን እንጠቀስ ዘንድ የዘመኑን ያህል በአዲስ እና ጠቃሚ ለሀገር ገንቢ በሆነ ሀሳብ እራሳችንን እናድስ ። አበቃሁ፤ ቸር ይግጠመን!አዲስ ዘመን መስከረም 2/2011ተገኝ ብሩ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=17890
[ { "passage": "እናንተዬ አውደ አመት ሲመጣ ምን ትዝ ይላችኋል? ዳቦው፣ ጠላው ቀጤማው … የምትሉ እንዳላችሁ አስባለሁ፤ ግን ደግሞ እነዚህ ሁሉ የአብዛኞቻችሁ እንጂ የሁላችሁም መልስ እንዳማይሆኑ እገምታለሁ። ዓመት በዓል ከእነዚህ ከምናያቸው ባለፈ የራሱ ድባብም አለው፤ በበአሉ አቅራቢያ ሰሞን ያለው የገበያ ግርግር እንዲሁም የእንኳን አደረሳችሁ ሰላምታና ስጦታ የበአል ልዩ ድምቀትና የአውደ አመት ገፀ በረከቶች ናቸው። መቼም ዓመት በዓል ምን ምን ይሸታል ብሎ የሚጠይቅ አይኖርም። ከድፎ ቅጠል እስከ ዶሮ፤ ከጠላ እስከ ጠጅ፣ ምን ይሄ ብቻ እጣኑ፣ ቀጤማው፣ ጠጅ ሳሩና ሌላውም ተደማምሮ አውደ ዓመት የራሱ መለያ ሽታ እንዳለው አመላካች ነው። ‹‹እና ይሄ ምን አዲስ ነገር አለው፤ ዘመናትን ያሳለፍንበት የኢትጵያዊነት መለያችን ነው›› የሚለኝ አይጠፋም። መቼም ለአንዱ ጥሩ ትዝታ ለሌላኛው ትርጉም አልባ ሊሆን ይችላል። ይሁንና በዓል ሲመጣ እኔን ስለሚያስገርመኝ ነገር ላውጋችሁ። ካለፉት ሶስት ዓመታት ወዲህ የእኛ ቤት በዓል አከባበር ሁለት መልክን ይዟል። ከዋዜማው እስከ በዓሉ እለት ያለው ሁነት የደስታችን ምንጭ ሲሆን፤ ከበዓሉ በኋላ ያሉት ተከታታይ ቀናት አንዳንዴም ሳምንታት ግን የጭንቃችን ምክንያት ሆነዋል። ለዚህ የሁለት አይነት ስሜቶች መፈጠር ምክንያት አለው። እህቴ የመተንፈሻ አካል ችግር (ሳይነስ) አለባት። ድሮ ህመሟ ጠንካራ አልነበረም፤ ብዙ ጊዜም እኛም ሆንን እሷ አናስታውሰውም ነበር። ከዓመታት በኋላ ግን ልጅ መውለዷን ተከትሎ ህመሙ እሷ ላይ ጠንከር ሲል የልጇ ደግሞ ይበልጡን ተባባሰ። የሚገርመው የሁለቱም ዋነኛ የህመም መነሻ ከበዓል በኋላ በየአካባቢው የሚጣሉ የእርድ ተረፈ ምርቶች ሽታ መሆኑ ነው። ታዲያ በዓል በመጣ ቁጥር የእኛ ቤተሰብ ቤትና ግቢ ብቻም ሳይሆን በሰፈሩ መንገድ ዳርቻ የተጣሉ ሽታ አምጪ ተረፈ ምርቶችን ማስወገድ ሆኗል። ግን ደግሞ ከየት እንደሚመጣ የማይታወቅ ነፋስ ይሄን ጦሰኛ እንግዳ ከየትም ብሎ እቤት ያደርሰዋል። እናም ከአብዛኛዎቹ በዓላት መጨረሻ ሆስፒታል መገኘት ለእኛ ቤተሰብ የግድ ከሆነ ከራርሟል። ለዚህም ይመስላል ለዓመት በዓል ‹ልብስ ይገዛልሻል› የተባለችው የአምስት ዓመቷ የእህቴ ልጅ ‹ዓመት በዓል መጣ እንዴ? በዓል እኮ መጀመሪያ ደስ ይላል፤ በኋላ ግን ደስ አይልም› ስትል የተደመጠችው። የዓውድ ዓመት\nሁለት መልክ ይሉሃል\nእንዲህ ነው። ለመሆኑ\nስንቶቻችን ነን እንደቀልድ\nእያወጣን የምንጥላቸው ቆሻሻዎችች\nሌሎችን ለችግር እንደሚያጋልጡ\nየምናውቀው?አዲስ ዘመን ሚያዝያ 15/2011", "passage_id": "4d7a7b1c6a01a19a7d04656df4302f3f" }, { "passage": "መሰለፍ በዝቷል፡፡ ለዳቦ፣ ለታክሲ፣ ለዘይትና ስኳር ኧረ ለምግብ ብፌም ጭምር መሰለፍ ግድ ሆኗል፡፡ ጊዜ የተረፈን ይመስል ሰዓታትን በሰልፍ ማሳለፍ ሳንወድ በግድ ለኛ የቀረበልን የየዕለት ገጠመኛችን ብሎም ተግባራችን ሆኗል፡፡ ዛሬ ስለ ዳቦና ዘይት ሸመታ ሰልፍ አይደለም የማውራው ወዳጆቼ፡፡ እሱማ ተብሎ ተሰለቸ ፤ ጭራሽ ተላምደነው ረስተንዋል እኮ፡፡ ይልቅ መንገድ ዘግተው መኪኖችን የሚያሰልፉ ምን አገባኝ ብለው ሰውን ብዙ ጉዳይ ውስጥ የሚያስገቡ መንገድ ዘጊዎች ላወራችሁ ነው፡፡ በእነርሱ ምክንያት መንገድ መድረሻችን ርቆን በእነርሱ ሰበብ ወደምንፈልገው መድረስ ያልቻልንና ስራችን ተበላሽቶብን ውስጣችን የደበነ ስንቶቻችን እንሆን? ታክሲ ውስጥ ነኝ፡፡ አጠገቤ የተቀመጠው ሰው እጅጉን መቸኮሉ ከሚለዋወጠው የስልክ ምልልስ ተረዳሁ፡፡ “እየደረስኩ ነው 10 ደቂቃ ብቻ፡፡” ይህን አረፍተ ነገር እሱን በመጠበቅ ላይ ላለና ለሚደውልልት ሰው እየደጋገመ ይመል ሳል። የታክሲው ተሳፋሪዎች አብዛኛዎቻችን መነሻችን አራት ኪሎ መዳረሻችን ደግሞ ሜክሲኮ ነው ፡፡ ታክሲው ከአራት ኪሎ ትምህርት ሚኒስቴር ህንፃ አለፍ እንዳለ ከፊት ለፊቱ አላነቃንቅ ያሉት የተሰለፉ መኪኖች ተከትሎ ይንፏቀቃል፡፡ አጠገቤ የተቀመጠው ደዋይ አሁንም ቃሉን ሳይለውጥ “አስር ደቂቃ ብቻ ታገሰኝ መጣሁ ማለቱን አላቋረጠም፡፡ የሰውዬው አስሬ ከኪሱ የሚጣራውን ስልክ እያወጣ በጣም ይቅርታ አሁን እየደረስኩ ነው አስር ደቂቃ ብቻ ማለት ማብዛቱ ካለው ሁኔታ ጋር አነጻጽሬ ግራ ገብቶኝ ይሄ አስር ደቂቃ ለውጥ ተደርጎበት ተሻሽሎ ይሆን እንዴ ብዬ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ በነገራችን ላይ ምንም ማደስ መለውጥ እና መቀየር ሲቻል የማይታደስ የማይለወጠው አንዴ ከመረሸ መመለስ የማይቻለው ጊዜ ብቻ መሆኑን ስንቶቻችን አስበነው ይሆን፡፡ ወደ ኋላ የለም በቃ፡፡ ካለው ላይ መቀነስ የነበረውን ትቶ ያልነበረ ላይ ማድረስ የጊዜ ተፈጥሮአዊ ኡደት ነው፡፡ ሰውዬው ቀጥሏል መጣሁ ደረስኩ አስር ደቂቃ…ወይ አስር ደቂቃ! እኮ ሜክሲኮ አይደለም ፍልውሀ ሳንደርስ ብዙ አስር ደቂቃዎች አለፉ፤ ተደምረው ሰዓት የሚሞሉ አስር አስር ብዙ ደቂቃዎች፡፡ ከወዲያኛው የስልክ ደዋይ ወይም ባለ ጉዳይ ደውሎ በማርፈዱ ምክንያት ትቶ በሆዱ ነገረው፡፡ ሰውዬው ተበሳጭቷል ያመለጠው ወሳኝ ጉዳይ መሆኑ ሁኔታው ያሳብቅበታል፡፡ ከታክሲው ወርዶ በእግር አይሮጥ አይደርስ ነገር፤ ታክሲውን አይታገስ ነገር ቆሟል፡፡ ወዳጄ ከወዳጁ ጋር ተቀያይሞ መቅረቱ አልያም ደግሞ ጉዳዩ ሳይሰምር መቅረቱ አናዶታል ። የሚጠብቀው ሰው\nቁጣ በተቀላቀለ ግሳፄ ሲናረውና ያሰበው ባለማሳካቱ ቆጨው፡፡ ያለመው ያለመስመሩ አበሳጨው፡፡ እዚያ መድረስ ያልቻለበትን ምክንያት ቢያቀርብ፣ ይቅርታ ቢጠይቅ፣ ቢያስረዳው ወይ ፍንክች፡፡ ከወዲያኛው ስልክ የሚሰማው የቁጣ ድምፅ የሰውዬውን ታጋሽነት እንዳውቀው አደረገኝ፡፡ ሰውዬው በስልክ የሚያወራውን ንግግር ለማስረዳት አልተቸገርኩም፡፡ የደዋዩ ድምፅ አጠገቤ ከተቀመጠው ሰው አልፎ በደንብ ይሰማኛል። ስልኩ የሚልከው ብቻ ሳይሆን የሚቀበለውም እንዳይመጥን የተደረገ ነው፡፡ እና ሰውየው ተሳድቦ ተሳድቦ ዘጋው፡፡ አጠገቤ ያለው ሰው የምር አሳዘነኝ፡፡ እሱም አለመታመኑም ያሰበው አለመሳካቱም አናዶታል፡፡ ወዶጆቼ ስንት ተመሳሳይ ገጠመኝ ገጥሞን በሁኔታውም ተማረን ይሆን፡፡ ከተማዋ ያልዋት መንገዶች በስርዓት መጠቀም አለመቻላችን ለትራፊክ መጨናነቁ አንድ ምክንያት ነው፡፡ አዲስ ያሏት መንገዶች ከሚርመሰመሱባት መኪኖች ጋር አለመግጠሙ ብቻ አይደለም ወዳጆቼ የተሳፈርንባቸው መኪኖች ተሰልፈው እያየን የማሳለፋችን ምስጢሩ፡፡ ይልቁንም መንገዶቹ በአግባቡ መምራት በሥርዓት የትራፊክ ፍሰቱን እንዲያሳልጡ ባለመድረጋቸው ነው፡፡ እርግጥ የመኪናው ቁጥር መጨመር የመንገዱ ውስን መሆን ለዚህ ችግር ማባባሻ ትልቅ ምክንያት መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡ አንዱ ጓደኛዬ ደጋግሞ ሲቀልድ እሰማ ዋለሁ ። እንዲሁ እንቶ\nፈንቶ አይደለም ቀልዱ ቁም ነገር የበዛው ለዛን የተላበሰ ቀልድ የሚቀልድ ነው። አንዳንዴ ቢያወሩ የማንሰለቻቸው ጥዑም ንግግሮችን የተካኑ ቢነገሩ የማይጠገቡ ወጎችን አዋዝተው የሚያቀርቡ አንደበተ ርቱዕ የሆኑ ሰዎች ይገጥሙናል፡፡ እንደዚያ ያለ ሰው ነው ወዳጄ፡፡ በሚከብዱ ነገሮች ላይ መቀለድ የሚወድ በዚያም ከባድ ነገሮችን አቅሎ የሚያይ፡፡ ቀላጁ ጓደኛዬ መኪና መግዛት አይደለም በቀን በታክሲ ብዙ ተመላልሶ ኑሮን መግፋት የከበደው ነው፡፡ ኑሮ አንዳይቀልድበት ቀድሞ ኑሮ ላይ ይቀልዳል፡፡ እንዲህ ነው መዳፈር ምን አባቱ የቀለዱበት ጉዳይ መቅለሉ አይቀር፡፡ ሰሞኑ የሆነ ስብሰባ ላይ አርፍዶ ተገኝቶ ለምን እንደዘገየ ተጠየቀ፡፡ “ያው አዲስ አበባ መኪና መንዳት ይከብዳል፤ መኪናዬ መንገድ ዳር ጥዬው አልመጣ ነገር መንገድ ተዘጋግቶብኝ በየት ልንዳ፡፡” የሱ ምላሽ ነበር፡፡ ከኔ በቀር ሁሉም የእሱን ምላሽና አሁን ያለው ሁኔታ አገናዝቦ ያላንዳች ምክንያት ጥርጣሬ ተቀበለው፡፡ አዲስ አበባ መንገዶችዋ ጠበው መሄጃ አጥሮ ብቻ እኮ አይደለም ይሄ ሁሉ የትራፊክ መጨናነቅ ውስጥ የገባችው፡፡ እነዚያን የበዙ ምክንያቶች ደግሞ መኪናው በሚፈለገው መልክ እንዳይጓዝ ሰራተኛውን የፈለገበት በሰዓቱ እንዳይደርስ አድርገውታል፡፡ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ከስራ የወጣን በትራፊክ መጨናነቁ እቤት የምንገባው አምሽተን የናፈቁን ልጆቻችን ጋር ሳንጨወት ደክመው ተኝተው ሆኗል፡፡ ውዶቼ አንዳንዴ መድረስ የፈለጋችሁበት ሳትደርሱ መገኘት ያለባችሁ ቦታ ሳትገኙ ታክሲ ውስጥ ቁጭ ብላችሁ ሰዓታት ያሰለፋችሁበት ጊዜ ትዝ ይላችኋል? ትዝ ይላችኋል ነው ያልኩት የኔ ነገር ያለንበትና የምንኖርበት እኮ ነው ምን ነካህ ካላችሁኝ ልክ ናችሁ፡፡ አንዳንድ ልክ ያልሆኑ ነገሮች ልክ እንዳንሆን ያደርጉናል፡፡ እናም ልክ ባልሆኑ መንገድ ብዙ ልክ የሆኑ ነገሮች ይናዳሉ፡፡ በተለይ የመንገድ መዘጋጋቱን ለማቅለል የሚሰራው የአዲስ አበባ መንገድ ትራፊክ ማኔጅመንት በትራፊክ መጨናነቅ የታወቁና ለጉዞ አስቸጋሪ የተባሉ መንገድና ቦታዎች ለይቶ ማሳለጥ እንዴት ከበደው፡፡ በየመሸታ ቤቱ በራፍ ላይ ተሰልፈው መንገዱ በመዝጋት ሌላን አላሳልፍ ያሉ እነርሱ ደግሞ በአንፃሩ እርፍ ብለው አልኮል በየአይነቱ የሚኮሞክሙ ግድ የለሾች ለምን መግራት አቃተው፡፡ አሁን አሁንማ አንዳንድ ሰፈሮች ላይ ቀን ሲያንቀላፉ ውለው ማታ የሚያብዱ ጉዳኛ የውስኪና መጠጥ ቤቶች ተበራክተዋል ። የመጠጥ ቤቶቹ\nደንበኞችም መኪናቸውን አሰልፈው መንገድ ዘግተው በማን አለብኝነት በካካታ ያመሻሉ፡፡ ለመንገድ ስርዓቱ አለመከበር ለትራፊክ ፍሰቱ አለመሳለጥ ትልቅ እንቅፋት የሚሆኑና ያልታወቁ በምክንያት ያልተለዩ ችግሮች እንደነዚህ በርክተዋል፡፡ ይህቺ ከአቅምዋ በላይ ብዙ ነገሮችን የተሸከመችው ከተማ የከተማነት ጥግ ላይ ማድረስ ከብዶን እኛን ጥግ ጥግ ማስያዝ ጀምራለች፡፡ ከፈለግነው ጋር ተገናኝተን በፈለግነው ሰዓት ጉዳያችን ላይ እንዳናወራ ካሻን ቦታ ተገኝተን የሚጠበቅብን እንዳንወጣ ያላትን አቅም ባለመጠቀማችን አቅም አሳጥታናለች፡፡ አዲስ እንደ ባህሪያችን አውላ እንደ አመላችን አሳድራ በሰፊው ሆድዋ ችላን ዛሬ ድረስ ደርሳለች፡ ፡ እኛው\nበሰራናት ልክ ገጽታዋ የምንመለከት ሰሪዎቿ ነን፡፡ ይህች የብዙኋን መዲና የስምዋን ያህል ባትዋብም የሚበቃንን ባይሆን የአቅምዋን ችራ ታኖረናለች፡፡ እኛ የምንሰጣት ነገር አንሶ ከእርሷ የምንጠብቀው በዝቶ እንጂ ለውጧንማ ማቅረብ እጅጉን በቀለለን ነበር፡፡ ይህቺ የኛ የሆነች ከተማ እንደራሳችን በኃላፊነት የምንይዛት እንደ ግል ጉዳያችን ማደግዋን የምንመኝና ለዚያም የምንታትር ቢሆን ከፍታ ላይ ባስገኘናትና እኛም በዚያ ውስጥ በዋኘን ነበር፡፡ ያላት ውስን ነገር በአግባቡ ባለመጠቀማችን እንቅስቃሴያችን ውስን እንዲሆን አድርጎብናል፡፡ ያሉትን መንገዶች ከኃላፊነት በራቀ ሁኔታ እየዘጋን ለኛ ስራ ስምሪት የሌላውን መዳረሻ ያራቅን ብዙዎች ነን፡፡ ዛሬ ላይ የመንገዱ መጨናነቅ ቀጠሮ እንዳ ናከብር ስራችንን በወጉ እንዳንወጣ አድር ጎናል ። መዳረሻው ርቆን\nበእግር አንሄደው ነገር ርቀቱ የማይሞከር ሆኖብን የቀጠርነው ሲቀር እየታዘብን ቀጥረውን ስንዘገይ እየታዘቡንም ቅያሜ ውስጥ ገብተናል፡፡ ስለራሳችን ምቾት ስንል የሌላን መንገድ መዝጋቱ ስለራሳችን ስምሪት ስንል ሌላውን መስመር ማሳጠቱ እስከመቼ ይቀጥል ይሆን፡፡ ለእያንዳንዱ ችግር\nመነሻ ተብሎ የሚጠቀስ\nቀጥተኛ የሆነ መነሻ\nከማሳየትና ከማየት ባለፈ\nትልቁን ችግር የፈጠሩ\nትንንሽ ችግሮች ላይ ትኩረት\nማድረግ ቢለምድብን የትልልቆቹ\nችግሮች መቆሚያ የሆኑ\nትንንሽ ችግሮች መቅረፍ\nየምንችል አይመስላችሁም፡፡ ውዶቼ\nመንገድ እንሁን ለዚያውም\nምቹ መንገድ፤ ሰዎች\nበተቃና መልኩ ተጉዘው\nወዳሰቡበት የሚደርሱበት ቅን መንገድ፡፡\nቸር እንሰንብት፡፡አዲስ ዘመን ነሃሴ 3/2011", "passage_id": "3385261c274ec26df56c4c3ca45d3faa" }, { "passage": "‹‹ እባብ ተንኮሉን አይቶ እግር ነሳው›› አሉ፡፡ እንዲያው ይህን ተንኮሌን አይቶ ድሃ አደረገኝ እንጂ እኔ ሀብታም ብሆን ኖሮ ለማስታወቂያ አምስት ሳንቲም አልከፍልም ነበር፡፡ የምር ግን በማስታወቂያ ስለተነገረ የሚገዛ ምርት አለ? እኔ ዕቃ ስገዛ ከሳሙና ጀምሮ ማስታወቂያ አይቼ አይደለም፤ ባይሆን እንኳን ከዚህ በፊት የተጠቀመበት ሰው ካለ ስለዚያ ምርት የሚያወሩትን ሰምቼ ነው፡፡ ምርትም ሆነ አገልግሎት በማስታወቂያ ሲነገር ‹‹ይሄን ነገርማ መግዛት አለብኝ›› ብዬ አላውቅም፡፡ ይሄ የኔ ባህሪ ነው፤ ምናልባት ማስታወቂያ ላይ በሚሰማው ጥራትና ጥንካሬ የሚገዛም ይኖር ይሆናል፡፡\nየሌሎች ማስታወቂያዎች ነገር ይቅርብንና እስኪ ስለ አልኮል ማስታወቂያዎች እንተዛዘብ፡፡ በእርግጥ ብዙ ተብሎላቸዋል፡፡ የሰሞኑን ለየት የሚያደርገው ግን የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ድረ ገጻቸው የለቀቁት የአልኮል ማስታወቂያን አስመልክቶ የወጣው ደንብ በማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ መነጋሪያ ሆኖ ነበር፡፡ በነገራችን ላይ ልብ ብላችሁ ከሆነ ይሄ ነገር በማህራዊ ገጾች መነጋገሪያ ሲሆን አንድ እንኳን ‹‹ለምን ይሄ ህግ ወጣ?›› ብሎ የተቃወመ አላጋጠመኝም፤ ቆይ ግን ሰው በአልኮል ማስታወቂያዎች ይህን ያህል ተማሮ ነበር ማለት ነው?\nበእርግጥ በወጣው ደንብ ላይ አንዳንድ ግልጽ ያልሆኑልኝ ነገሮች አሉ፡፡ እንደሚታወቀው ከአልኮል ማስታወቂያዎች ውስጥ አብዛኞቹ የቢራ መጠጦች ናቸው፡፡ እነዚህ የቢራ መጠጦች ደግሞ የአልኮል መጠናቸው ከአምስት በመቶ በላይ አይደለም፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ እንዳሉት ግን የአልኮል መጠጥ አምራቾች፣ አስገቢዎችና አከፋፋዮች በስፖርት ማዘወተሪያ ቦታዎች፣ በትምህርት ቤቶች፣ በህዝብ በዓላትና በዓውደ ርዕይ ቦታዎች የአልኮል መጠኑ ከ10 በመቶ በላይ ማስታወቂያ እንዳይሠራ ነው፡፡\nየቦታዎቹ ነገር በጣም ደስ ብሎኝ ነበር፤ የአልኮል መጠኗ ነገር ግን ምቹ አይደለችም፡፡ ክቡር ሚኒስትር ይሄን ነገር እንደገና ቢያስቡበት ጥሩ ነው፡፡ ይሄ ማለት እኮ እነ ቢራ በተጠቀሱት ቦታዎች መተዋወቅ ይችላሉ ማለት ነው፡፡ የሆነውስ ሆነና ግን ከ10 በመቶ በላይ የአልኮል መጠን ያለው መጠጥ ምን ይሆን? ይሄ ነገር የሀበሻ አረቄ ትሆን እንዴ? ለነገሩ አረቄ በፋብሪካ ስትጠመቅ ዘሮቿ ብዙ ብዙ ይሆናሉ። እነሱን አለማየትም አንዱ እፎይታ ሊሆን ይችላል።\nቆይ እስኪ የሚኒስትሩን መመሪያ እንቋጨው! ሚኒስትሩ ቀጥለው ደግሞ እንዲህ ይላሉ፡፡ «የአልኮል መጠኑ ከ10 በመቶ በታች የሆነ የትኛውም የአልኮል ማስታወቂያ ከምሽቱ 3፡00 ጀምሮ እስከ ንጋት 12፡00 መተላለፍ ይችላል›› ይቺኛዋ ጥሩ መመሪያ ናት፡፡ ከምሽት ሦስት ሰዓት በኋላ ከ18 ዓመት በታች የሆኑት ስለሚተኙ ቢያንስ ይሻላል፡፡ በዚችኛዋ ሰዓት ነበር አረቄን ማስተዋወቅ! እንዲያው ቢያንስ ቢያንስ ይቺን ግጥም እንኳን ቢለቋት።\n«አረቄ ጠጥቶ አረቄ ነው ሽታው\nይታመማል እንጂ ሰው እንደ በሽታው!»\nአይ የገጠር ልጅ ነገር! ይቺን አረቄ ደጋገምኳት አይደል? ታዲያ ምን ይደረግ እኔ በአካባቢዬ የማውቀው የአልኮል መጠጥ አረቄ ብቻ ነበር፤ አሁን ባልጠጣው እንኳን ባለፍኩበት ጎዳና ሁሉ በትልቅ ባነር፣ በገባሁበት ካፌ ሁሉ በቴሌቪዥንና ሬዲዮ፣ ባለፍኩበት ጎዳና ሁሉ በየግሮሰሪው የመጠጥ ዓይነት አያለሁ፡፡ የአረቄን ነገር አረቄ ያነሳዋልና የአካባቢያችን አረቄ ጠጪዎች የሚቀኟት ይቺ ቅኔ ትዝ አለችኝ፡፡\n«ታረቂው እባክሽ ታረቂው\nተይ አታስጨንቂው»\nበገጠርኛ ዘዬ ‹‹ታረቂው›› የሚለውን ‹‹ከአረቄው›› ብለን እንተረጉመዋለን(የትኛው ነው ትክክል ሌላ ጥያቄ ነው)፤ እናም አረቄ ቅጅልኝ ማለት ሲፈልጉ ‹‹እባክሽ ታረቄው›› እያሉ ያንጎራጉራሉ፡፡ የቅኔዋ ሰም ይሁን ወርቅ ባላውቅም ሁለተኛው ትርጉም እርቅ አድርጊለት ለማለት ነው፡፡\nከአረቄ ወሬ ወጥተናል (ኡኡቴ! አልሸሹም ዞር አሉ)፤ ከአረቄ ወሬ ወጥቶ ወደ ቢራ መሄድ ምን ይሆን ልዩነቱ? የሆነውስ ሆነና የአልኮል መጠጦች ማስታወቂያ ገደብ ይደረግለት መባሉ ጥቅሙ ለማን ይሆን? እንደኔ እንደኔ የአልኮል ማስታወቂያ ጭራሹንም ቢከለከል ራሱ ጥቅሙ ለባለቤቶች ነው፡፡ በቃ ወጪ ይቀንሳሉ፡፡ ማስታወቂያው በመቅረቱ ምንም የሚጎልባቸው ነገር የለም፡፡ ማስታወቂያ ቀረና ይሄ ህዝብ መጠጣት ሊያቆም? በፍጹም አይታሰብም! እንኳን የማስታወቂያው መከልከል መጠጣት ቢከለከል ራሱ አይተወውም፡፡\nበነገራችን ላይ የመጠጥ ፋብሪካዎች የተለያዩ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞችን ስፖንሰር የሚያደርጉት እዚያ ላይ በመተዋወቁ ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት ብቻ አይደለም፡፡ ማህበራዊ ኃላፊነትን እንደመወጣትም ይቆጥሩታል፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ፋብሪካዎች ድጋፍ ባያደርጉ ያ ፕሮግራም ወደ ህዝብ ሊደርስ አይችልም፡፡ ዋናው ነገር ያ የሚተላለፈው ፕሮግራም ይዘት ነው፡፡ ህብረተሰቡን የሚያስተምር፣ ታሪክና ባህልን የሚያስተዋወቅ ፕሮግራም ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲህ ዓይነት ፕሮግራሞችን የሚደግፉ የታወቁ የቢራ ፋብሪካዎችም አሉ፡፡\nእነዚህ ድጋፍ የሚያደርጉ የቢራ ፋብሪካዎች ህብረሰተሰቡን እያገለገሉ እንደሆነ ነው የሚሰማቸው፡፡ አስታውሳለሁ 2009 ዓ.ም ሄኒከን ቢራ ፍብሪካ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ አንድ የቅሬታ ደብዳቤ ጽፎ ነበር፡፡ ስለፋብሪከው በተሠራው ዘገባ ላይ ቅሬታውን ሲገልጽ የተለያየ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ ገልጾ ነበር፡፡ ያ ማለት ስፖንሰር ከሚያደርጋቸው የሬዲዮና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች በተጨማሪ የተጎዱ ወገኖችንም ይደግፍ ነበር ማለት ነው፡፡\nእኔ ራሱ ማስታወቂያ ሠራሁላቸው እኮ! ይህን ማለት የተገደድኩበት ምክንያት ስፖንሰር የሚሆኑት ማስታወቂያውን ሰምቶ ተጨማሪ ጠጪ እናገኛለን ብለው ስለማይሆን ነው፡፡ እናም ይሄ የማስታወቂያ ደንብ ቢጸድቅና ቢተገበር በፍጹም እነዚህ የመጠጥ ፋብሪካዎች አይጎዱም (እንዲያውም ተገላገሉ)፡፡ እኛም ተገላገልን! የእኛ ግልግል ደግሞ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ላይ ያለውን ቅጥ ያጣ ጩኸት መገላገል ነው፡፡ እንደ መጥጥ እና ኮንዶም ማስታወቂያ የሚያሳቅቀኝ የለም፡፡ ወዲያውኑ አቀራረቡ ተቀየረ እንጂ አንድ በሬዲዮ የሚተላለፍ የኮንዶም ማስታወቂያ ነበር፡፡ ገና ሲጀምር ብቻዬን ሆኜ አፍራለሁ፡፡ የህዝብ ትራንስፖስር ውስጥ የሰማው ሁሉ ግማሹ ይናደድ ነበር፤ ግማሹም ይስቅ ነበር፤ ግማሹም አፍሮ እንዳልሰማ ሆኖ የሚያሳልፈው ነበር፤ በቃ ፖርኖግራፊ እንደማሳየት በሉት!\nየአልኮል ማስታወቂዎችም እንደዚሁ ነው፤ ከሰው ጋር ሆኖ ለማየት የሚያሳፍር፡፡ ምንም እንኳን በማስታወቂያ ውስጥ ግነት ስለሚበዛ የሰዋሰውም ሆነ የተጠይቅ ህግ ባይጠበቅም አንዳንድ ጊዜ የማይሆን ነገር ሁሉ ያሳያሉ፡፡ ለምሳሌ ሽማግሌ የተጣላ ሲያስታርቅ፤ ሰካራም ሲመክር እንጂ ሽማግሌ አልኮል ሲያስተዋውቅ የሌለ ነገር ነው፡፡ በሴቶች የሚተዋወቀው የአልኮል መጠጥም መስመሩን የሳተ ነው፡፡ በመጠጥ የሚታወቅ ወንድ እንጂ ሴት አይደለችም፤ ሴት መጠጥን ስትጠላ ነው በገሃዱ ኑሯችን የምናውቀው፡፡ በየአደባባዮች ላይ የተሰቀሉ የመጠጥ ባነሮች ግን የተራቆተች ሴት መጠጥ ጨብጣ ነው፡፡ የሚጠጡ ሴቶች የሉም እያልኩ አይደለም፡፡\nለማንኛውም የዚህ የማስታወቂያ ደንብ መውጣት ማንንም ስለማይጎዳ ተግባራዊ ይደረግልን!ዋለልኝ አየለ", "passage_id": "de9fe1ce32ad37933ba9fba8fa1251be" }, { "passage": " መርካቶ እንደወትሮው ሁሉ ሞቅ ደመቅ ብላለች። ከዕለት ጉርስ ፈላጊ ተባራሪ እስከ ሲራራ ነጋዴ ተሰይመዋል። ዛሬም በህዝብ ትርምስ ሰከንዶች፣ ደቂቃዎች፣ ስዓታትና ቀናት ይነጉዳሉ። ሰዎች ተቃቅፈው ይሄዳሉ። ተሰብስበው ያወራሉ። ቅርብ ለቅርብ ሆነው ዋጋ ይከራከራሉ። በመኪና እና በሰው በተጨናነቀው ጎዳና እየተጋፉ ይተላለፋሉ። ይጨባበጣሉ። እጃቸውን ከምላሳቸው እያነካኩ ብር ይቆጥራሉ፤ ይቀባበላሉ። የመርካቶ ደንበኞች ኮሮና ኢትዮጵያ መግባቱን ቢሰሙም አልሰሙም። ጥንቃቄ ወዲያ ያሉ ይመስላሉ።ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ፣እጅን መታጠብ፣ ባልታጠበ እጅ ዓይን፣ አፍና አፍንጫን አለመነካካት፣ የፊት መሸፈኛ ማስክ ማድረግ፣ …የሚሉና ሌሎች የህክምና ባለሙያዎች ማስጠንቀቂያዎች ለእዚያ አካባቢ የሙዚቃ ያህል ነው። ዛሬም በመርካቶ ኮሮና ከመምጣቱ በፊት የነበረው ሂደት እንደቀጠለ ነው። ይሄ ያሳሰባቸው በጎ አድርጊዎች ደግሞ በመኪና ሆነው በድምጽ ማጉያ “ከኮሮና ቫይረስ ራሳችሁን ጠብቁ” ሲሉ ይወተውታሉ። የኮሮና ወረርሽኝ ስርጭት እየሰፋ ከሄደ መርካቶ የኮሮና ማሰራጫ ማዕከል እንደምትሆን እንቅስቃሴዋ ይናገራል። ለአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን ወደ የክልል አከፋፋይ እንደምትሆን አሁን የሚታየው ገጽታ ይመሰክራል።በቦታው ተገኝቼ ያነጋገርኳቸው ሰዎችም የነገሩኝ መንግሥት አስፈላጊውን የእርምት ዕርምጃ የማይወስድ ከሆነ መርካቶ ትልቅ የስጋት ቦታ ይሆናል ሲሉ ነው። የመርካቶ ነጋዴ የሆኑት አቶ መሀመድ ረሽድ፤ በመርካቶ ኮሮናን በመከላከል ከፍተኛ መዘናጋት ይታያል ይላሉ። የኮሮና ቫይረስ ኢትዮጵያ ገባ ተብሎ መጀመሪያ አካባቢ ሲነገር የመደናገጥና የመጠንቀቅ ዓይነት ምልከት ታይቶ ነበር። አሁን ግን ነጋዴውም ሆነ ሸማቹ ወደ ድሮው መመለሱን ይገልጻሉ። ይህም ቫይረሱን ከአዲስ አበባ በቀላሉ ወደ ክልሎች ሊያሰራጭ እንደሚችል ይናገራሉ። በመንግሥትና በበጎ አድራጊዎች በሽታውን ለመከላከል የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ ቢሠራም የባህሪ ለውጥ አልመጣም። በየቀኑ አዳዲስ ተጓዦች ስለሚመጡም ለውጥ ለማምጣት አስቸጋሪ መሆኑን በማንሳት መንግሥት ከማስተማር ጎን ለጎን አስገዳጅ ዕርምጃዎችንም መውሰድ እንደሚገባው ጠቁመዋል። በመርካቶ አውቶቡስ ተራ ወደ ደብረማርቆስ ለመሄድ አውቶቡስ ሲጠብቅ ያገኘነው ወጣት መኳንንት ቀለመወርቅ፤ ከአውቶቡስ ተራ ውጪ ያለው ከፍተኛ የህዝብ መጨናነቅና ገፊያ ለቫይረሱ ያጋልጣል የሚል ስጋት ደቅኖበታል። በአውቶቡስ ተራ ውስጥ ግን አካላዊ ርቀት እንዲጠበቅ የሚደረግ በመሆኑና የእጅ ንጽሕና መጠበቂያም ስለሚሰጥ ጥንቃቄው ጥሩ መሆኑን ያነሳል። በሽታውን ሙሉ ለሙሉ ለመከላከልም አሁንም የባህሪ ለውጥ ማምጣት የግድ መሆኑን ይናገራል። በስፍራው በመኪና ላይ በድምፅ ማጉያ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ ሲሠራ ያገኘሁት የኢትዮጵያ ስካውት ማህበር አባል ወጣት ብሩክ መሰለ፤ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቱ ቢሰጥም የባህሪ ለውጥ በማምጣት ዙሪያ ብዙ እንደሚቀር ይገልጻል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን እንደቀላል የመቁጠር ሁኔታ ይስተዋላል ብሏል። በፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን የአዲስ ከተማ አገር አቋራጭ መናኸሪያ ኃላፊ አቶ ደረጀ ሞገስ እንዳሉት፤ በሽታው በኢትዮጵያ ከተከሰተ በኋላ የተሳፋሪውን ቁጥር በግማሽ በመቀንስ፣ ወደ ውስጥ ሲገቡ ሙቀት በመለካት፣ እጃቸውን እንዲታጠቡ፤ ርቀታቸውን ጠብቀው አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ እየተሠራ ነው። ሆኖም ለ15 ቀናት መንገድ መዘጋቱና የፋሲካን በዓል ተከትሎ መምጣቱ ከፍተኛ መጨናነቅ መፍጠሩን ይናገራሉ። የቢሮውን ሥራ ሙሉ ለሙሉ አቁመው ተገልጋዮች እያስተናገዱ ሲሆን በግቢው ውስጥ ቫይረሱ እንዳይተላለፍ እያስተካከሉ ቢሆንም ከግቢው ውጪ ግን ስርዓት ለማስያዝ አስቸጋሪ መሆኑን ይናገራሉ። ከግቢው ውጪ ያለውን ትርምስ ለመቆጣጠር አስቸጋሪ ነው። ህብረተሰቡ ምክረ ሃሳቡን ተግባራዊ እያደረገ አይደለም። ህዝቡ መለወጥና እራሱን መጠበቅ ካልቻለ ለውጥ አይመጣም ሲሉ ገልጸዋል።\nአዲስ ዘመን ሚያዝያ 18/2012\n አጎናፍር ገዛኽኝ", "passage_id": "a846f5a2e39e48ca87cb8a5aaaaacb62" }, { "passage": " የመላመድ\nአባዜበአገራችን የኮሮና ወረርሽኝ መከሰቱ ከታወቀበት ጊዜ ጀምሮ የመረዳዳት ባህላችን አንድ ደረጃ ከፍ ሲል ተፋዞ የነበረው ማህበራዊ መደጋገፋችንም እንዲያንሰራራ ዕድሉን አግኝቷል፡፡ በዋናነት በወቅታዊው ጉዳይ ሥራቸውን ላጡ፣ ለተቀዛቀዘባቸውና ለአቅመ ደካሞች አስፈላጊውን ሁሉ ለመደጎም በርካታ ግለሰቦችና ድርጅቶች ድጋፍ ሲያደርጉ እያስተዋልን ነው፡፡ ይሄ የሚያስመሰግን ተግባር ነው፡፡ እውነታው ይሄ ቢሆንም ግን አንዳንድ የሚያሳዝኑ ነገሮችንም ከበጎ ተግባሩ ጎን ለጎን አብረን መታዘባችን አልቀረም፡፡ ለእርዳታ የቀረቡ ዕቃዎች ርቀታቸውን ጠብቀው የሚወስዳቸው ሰው ያስፈልጋቸዋል፡፡ ሆኖም በተግባር የተመለከትነው በአንዳንድ የድጋፍ መስጫ ቦታዎች ሰዎች ጥንቃቄ ካለማድረጋቸውም በላይ የእርዳታ አስተባባሪዎች አቅመ ደካሞችን ሲጨብጧቸው ነው። ይሄን መመልከት ጥሩ ስሜት አይፈጥርም፡፡ ይህን ስንመለከት «በቃ! ኮሮናን ተላመድነው» የሚል ጥያቄ ይደቅንብናል። ጎበዝ መዘናጋት ይቅርብን እንጂ፡፡ እርዳታ ስናደርግ በሽታ አብረን እንዳንለግስ መጠንቀቅን አንዘንጋ፡፡ ጥረታችን «ግንጥል ጌጥ» አይሁንብና። ይህ ብቻ አይደለም ብዙዎቻችን ቀደም ሲል እናደርገው የነበረውን ጥንቃቄ አቁመናል፡፡ ተዘናግተናል። በየቀኑ በርከት ያለ የኮሮና ተጠቂ ቁጥሮች ሪፖርት ሲደረጉ የምንሰማ ቢሆንም ደንገጥ ብሎ ተገቢውን የጥንቃቄ እርምጃ የሚወስደው ሰው እየቀነሰ ነው፡፡ እርግጥ ነው ይሄ የመዘናጋት ጉዳይ በእኛ ማህበረሰብ ውስጥ የሚታየው በኮሮና ወረርሽኝ ላይ ብቻ ሳይሆን ሁሌም አዳዲስ ነገሮች ሲከሰቱ ጭምር ነው። መርሳት ሳይኖርብን ከአንድ ሳምንት በኋላ የተላመድናቸው ነገሮች በርክተዋል፡፡ እስኪ አብነት እናንሳ። ለቀናት ሲያከራክር የነበረው የአልኮል መጠጥ ዋጋ ጭማሬ ዛሬ ምን ደረጃ ላይ ነው። በወቅቱ ቢራና የመሳሰሉት መጠጦች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ሲደረግ «እንዴት ይህ ሊሆን ይችላል?» በማለት የተቃወሙ ብዙዎች እንደነበሩ እናስታውሳለን። የፋብሪካ ባለቤቶችም «ተጠቃሚ አይኖርም፤ ፋብሪካችንን ልንዘጋ እንችላለን በውስጣችን ያሉ ሠራተኞችም ይበተናሉ…» ሲሉ ተደምጠው ነበር። እውነትም ለጊዜውም ቢሆን በርካታ ግሮሰሪዎች ቀዝቅዘዋል፡፡ አንድ ሁለት ብለው የሚገቡ ደንበኞች በጊዜ ወደ ቤታቸው (እያጉረመረሙም ቢሆን) ገብተዋል። አላስችል ያላቸው ከኮታቸው ቀንሰው ከሁኔታው ጋር እራሳቸውን ለማላመድ ጥረት ሲያደርጉ ተስተውለዋል። ከሳምንት በኋላ የተፈጠረው ግን ተቃራኒው ነው። ሁለት የምጠጣበትን አንድ፣ አራት የምጠጣበትን ሁለት ወዘተ እያሉ መጠጣት የጀመሩ ደንበኞች ከቀን ወደ ቀን ቃላቸውን እየሰበሩ በመምጣታቸው የመጠጥ ቤቶች በድጋሚ ወደነበሩበት ቦታ ተመለሱ። አፈር ነህና ወደ አፈር … ይሏል ይሄኔ ነው። ፍርሃት ሲያንዘፈዝፋቸው የነበሩ የአልኮል ፋብሪካዎች፣ ደንበኛ ስላጣሁኝ ሥራዬን አቁሜያለሁ ብለው ሪፖርት ያደርጋሉ ተብለው የተጠበቁ መጠጥ ቤቶች በፌሽታ ተሞሉ። ሁሉም ወደ ቀድሞው ሁኔታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተመለሳ፡፡ ዛሬ ላይ ማንም ሰው የመጠጥ ዋጋ አያሳስበውም። በየመጠጥ ቤቶች የሚታየው ሰው ለዚህ ምስክር ነው፡፡ ድርጅታችን ይዘጋል፤ ሠራተኞቻችን ይበተናሉ ያሉ ሁሉ አሁን ተረጋግተዋል። ድራፍቱን በእስትሮ እያሉን ነው። ይሄ ታዲያ የመልመድ አባዜ ማሳያ አይሆን ይሆን? አሁንም እየተስተዋለ ያለው በቀላሉ ወረርሽኙን የመላመድ ሁኔታ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለበሽታው መስፋፋት መልካም አጋጣሚን ፈጥሮለታል፡፡ የኮሮና ወሬ አዲስ እንደሆነ አካባቢ ሁሉም ሰው በቤት ውስጥ መዋል ጀምሮ ነበር፡፡ አብዛኞች የከተማችን አውራ መንገዶች ሰው አልባ መሆን ችለው ተመልክተናል፡፡ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ የከተማችን አውቶቡሶች ትኬት ሻጩና ሹፌሩ ብቻ ሲመላለሱ ለጥቂት ቀንም ቢሆን ታዝበናል፡፡ ነገር ግን ብዙም ሳይቆዩ በሁለት ሰዎች መካከል አንድ ወንበር ክፍት አድርገው ወደ ማጓጓዝ ተሸጋገሩ፡፡ አሁን ይሄ ተቀይሯል። በወንበሮች ሙሉ መጫንን ተለማምደዋል፡፡ እንዲሁም ከኮሮና ጋር ከመላመዳችን በፊት ወደ አውቶቡስ ውስጥ የሚገባ ሁሉ እጅ ማፅጃ ይደረግለት ነበር፤ አሁን ይሄ ቀርቷል። ኮሮናን ተላመድነው ማለት አይደል። እሱ ግን ቂም በሆዱ ቋጥሮ ሥራውን ቀጥሏል። ታክሲዎችም የወጣውን አዋጅ ተከትለው ከስድስት ሰው በላይ አይጭኑም ነበር፡፡ በሽታውን ከተላመዱ በኋላ ግን መጠንቀቁና ሕግ ማክበሩ ለጊዜው ብቻ መሆኑን የወሰኑ ይመስላሉ። ሕግ አስከባሪ መኖር አለመኖርን እየተጠባበቁ አንድ ሰው ወደ መደረብ መሸጋገራቸውን በዓይናችን አይተናል። ምን ይሄ ብቻ መንገዶችም በሰዎች ተሞልተዋል፡፡ በርካታ የምግብና የመጠጥ ቤት አስተናጋጆች በኮሮና ምክንያት ተጠቃሚ አጥተው አብዛኛውን ጊዜያቸውን በድብርት ነበር የሚያሳልፉት፡፡ ይሄ ወረርሽኙ በቁጥጥር ስር እስኪውል አልቀጠለም፡፡ አሁን ምግብና መጠጥ ቤቶች መቀመጫ እስኪጠፋ ድረስ በሰዎች ተጨናንቀዋል። አስተናጋጆችም እንኳን ሊደበሩ ቁጭ የሚሉበት ጊዜ የላቸውም፡፡ አስፈሪው ነገር ግን ወረርሽኙ እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ አለመምጣቱ ነው፡፡ ታዲያ ይህን ቅብጠት ምን ልንለው እንችላለን? የመላመድ አባዜ? የመዘንጋት እና የመላመድ ተግባራትን ልናርቅ ይገባል። ቢያንስ ቢያንስ የቢራ ዋጋ መናሩን መልመዳችን አይከፋም። ኮሮናና መጠጥ ለየቅል ናቸው፡፡ ኮሮናን መልመድ በዚህ ምድር ላይ የመቆየት ያለመቆየት እጣፈንታችንን ይወስናል፡፡ አሁን አሁን እንደ በፊቱ እጅን በፍጥነት መታጠብም አቁመናል፡፡ አንድን ነገር እንዲህ በቀላሉ መልመድ ከቻልን ምን አለበት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን፣ መተሳሰብን፣ አብሮ በጋራ መኖርንና በጥቅሉ የዕለት ተዕለት ኑሮአችንን የሚያቀሉልንን ነገሮች መልመድ ተሳነን፡፡ ሁኔታው ትንሽ ግራ ያጋባ ይመስላል። አእምሯችን የተከለከለውን እንደሚፈልግ ሕፃን ልጅ፤ ከሚጎዳን እንድንላመድ ይገፋፋናል። ወዳጄ ጊዜው ከኮሮና ጋር መላመድ ሳይሆን መጠንቀቅ ይጠይቃል። ባላወቅነው ጸባይ እጅ ከምንሰጥ እዚያው በሩቁ ብለን ብንራራቅ ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገም ይበጃል፤ የትራንስፖርት አጠቃቀማችንም ይስተካከል፡፡ የግዴታ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር እንቅስቃሴያችን በቤታችን ይገታ፡፡ ከኮሮና ጋር ሳይሆን እቤት ከመዋልና ከመጠንቀቅ ጋር እንላመድ፡፡ ሰላም! ሞገስ ፀጋዬ ከእርሶ ለእርስዎ ቤት መዋል ከጀመርኩ ጀምሮ እየወፈርኩ ነው ምን ትመክረኛለህ? ቤዛዊት ለማ (ከሳሪስ) መልስ፡- ከምትበይው ለሌሎች አካፍዪ ግብፅ ወደ ድርድሩ የተመለሰችው ለምን ይመስልሀል? ሙሉጌታ ተገኝ (ከመርካቶ) መልስ፡- ጣሊያን መክራት ከምግብ የሚጥምህ ምን ዓይነት ነው? ሳቤላ (ከ4 ኪሎ) መልስ፡- ተጋብዤ የምበላው ማንበብ አልወድም ግን ደግሞ ብዙ መፃፍ እፈልጋለሁ ምን ላድርግ? ወርቅነህ ቱፋ (ከአዳማ) መልስ፡- መሰረት የሌለው ቤት ልትሰራ አስበሀላ ኮሮና በዚሁ ከቀጠለ ምን ልታደርግ አሰብክ? ሙሉ ሰው (ከጎንደር) መልስ፡- መደበቅ ኮሮና እንደገባ በየመንገዱ እጅ ሲያስታጥቡ የነበሩ ልጆች የት ሄዱ? መልስ፡- ውሃ ፍለጋ የፊት ጭንብል ሁሉም ካደረገ እኔ ሳላደርግ ብዞር ኮሮና ሊዘኝ ይችላል? ቶማስ ነኝ (ከቤላ ) መልስ፡- የዚህን መልስ እንኳን እኔ ኮሮናም አያውቅ የኮሮና የቅርብ ወዳጅ ማን እንደሆነ ታውቃለህ? ዘላለም ዘርጋው (ከካራ) መልስ፡- መዘናጋት አሜሪካ ግን የዴሞክራሲ መብት እኔ ጋር ተረጋግጧል እያለች፤ በጥቁሮች ላይ የሞት መከራ ለምን ይደርሳል? ኢሳያስ ሞጆ (ከባህርዳር) መልስ፡- ዴሞክራሲ ተረጋግጧል ነው ተረግጧል ያለችው? እስኪ አረጋግጥ በትርፍ ሰዓትህ አብዝተህ የምታደርገው ምንድነው? መልስ፡- እጄን መታጠብ ተገኝ ብሩ አስደናቂ እውነታዎችወፎች አይሸኑም፡፡ • ጉንዳኖች ፈፅሞ አይተኙም፤ሳንባ የላቸውም፤ • ጉንዳን እስከ 7 ዓመት ሊኖር ይችላል ንግስቷ ግን እስከ 15 ዓመት ልትኖር ትችላለች:: • ሻርክ ብቸኛው የማይታመም እንስሳ ነው። ምንም ዓይነት በሽታ አያጠቃውም ካንሰርን ጨምሮ:: • ፈረሶች እና ላሞች ቁመው ነው የሚያንቀላፉት:: • የማር ንብ ሁለት ሆድ ሲኖራቸው አንዱ ለማር ሲሆን ሁለተኛው ለሚመገቡት ምግብ ማስቀመጫ ያገለግላቸዋል:: • ትልቁ ነጭ ሻርክ ከሦስት ወር በላይ ሳይበላ መጓዝ ይችላል:: • አብዛኞቹ ዝሆኖች በክብደት ከሰማያዊ ዓሣነባሪ (Blue whale) ምላስ ያንሳሉ:: • በረሮ በረሀብ እስኪሞት ድረስ ለሳምንት ያህል ጭንቅላቱ ተቆርጦ በሕይወት መቆየት ይችላል:: • የአህያ ዓይን አቀማመጥ በአንድ ጊዜ አራቱንም እግሮች ማየት ያስችሉታል:: • ዶልፊን ውሃ ውስጥ ከ24ኪ.ሜ ርቀት ያለ ድምፅ በቀላሉ መስማት ይችላል:: • የወባ ትንኝ (Mosquito) 47 ጥርስ አላት:: • ማንኛውም ሁለት የሜዳ አህያ(zebra) አንድ ዓይነት መስመር አይኖራቸውም:: • ቢራቢሮ የሚቀምሱት (taste) በኋላ እግራቸው ነው:: • የወንድ ሸረሪት የወሲብ አካል በአንዱ የእግሩ ጫፍ ላይ ይገኛል:: • ንቦች አምስት ዓይን አላቸው:: • አሳማ በተፈጥሮ(physical) ወደ ሰማይ ማየት አያስችለውም:: • አይጥ ከተራበች የራሷን ጅራት ትበላለች። • ለሚስቱ ታማኝ የሆነ እንስሳ ቀበሮ ብቻ ነው። • ሰማያዊ ዓሣነባሪ (Blue whale) በመጠን እስካሁን በዓለማችን ከነበሩ እና ካሉ እንስሳዎች ትልቁ ነው:: • የሌሊት ወፍ ብቸኛዋ ከአጥቢዎች መብረር የምትችል ስትሆን የእግር አጥንቶቿ ከመቅጠናቸው የተነሳ መብረር እንጂ መራመድ አይችሉም:: • የሌሊት ወፍ ምንጊዜም ከዋሻ ሲወጡ ወደ ግራ ይበራሉ:: • እባብ ዓይኖቹ ቢከደኑም በዓይኖቹ ቆብ ማየት ይችላል:: • ወንድ የወባ ትንኝ አይናደፍም ሴቷ ብቻ ናት መናደፍ የምትችለው:: • የዱር አይጥ በፍጥነት መራባት የሚችሉ ሲሆን በ18 ወራት ብቻ 2 አይጦች 1 ሚሊዮን ዘመዶችን ማፍራት ይችላሉ:: • አንድ ንብ አንድ የሾርባ ማንኪያ ማር ለማዘጋጀት ከ4000 በላይ አበቦችን መጎብኝት አለባት:: • ቀንድ አውጣ ለ3 ዓመት መተኛት ይችላል:: • አንድ ላይ የተያያዘ የሸረሪት ድር ተመሳሳይ ወፍረት ካለው አንድ ላይ ከተያያዘ የብረት ሽቦ ይጠነክራል:: • ዝሆኖች ከ3ማይል ላይ ያለ ውሃ ማሽተት ይችላሉ:: • ኦይሰትር የተባለ የዓሣ ዝርያ ከአንዱ ፆታ ወደ ሌላኛው እንዲሁም ወደ ነበረበት ለወሲብ በሚመቸው • ፆታውን መቀየር ይችላል:: • በየዓመቱ 1/3 የሚሆነው የዓለማችን ሰብል በተባይ/ ነፍሳት ይወድማል:: • ምንጭ ፡-New Information  ዲጂታል የኔቢጤ ‹‹ጎፈንድሚዎች›› ሰው ከክብሩ ወርዷል። ሂሳዊና የሞራል ውድቀት የገጠመው በዝቷል። ከልክ ያለፈ ራስ ወዳድነት ተጭኖ በግል ፍላጎቱ የናወዘውን ቤት ይቁጠረው። ሙሉ አቅሙን ለጥፋት፤ ለቅጥፈት ያውለዋል። ይገርማል! ደግሞ በዚህ ቢያበቃ ጥሩ። ክፋት እንዴት እንጀራ ይሆናል? ቁጭ ብሎ ነገር እንደ ዳንቴል እየጠለፈ፤ ሌላው ለግብሩ ይከፈለዋል። ረብጣ ገንዘብ በባንክ ደብተሩ ውስጥ ሰተት ብሎ ይገባለታል። ስለተንኮል ፀልዮ ጠዋት ከአልጋው ይነሳል። ለክፋት ይበላል፤ ለእኩይ ያጌጣል። ይገርማል! ምን እሱ ብቻ…ልቦናው የታወረውስ? መልካሙን የሚጠየፍ፤ ለጥላቻ ጆሮው ክፍት። እርሱም እንደሌላው ዓይኑን በአይበሉባው እያሸ በግራ ጎኑ ይነሳል። ድሮ ድሮ እጁ ለስንፍና የቀረበ፤ በየጥጋጥጉ ምእመን አጭበርብሮ ሆዱን ይሞላ ነበር። ይሄ በየመንገዱ የምናየው ሃቅ ነው። ለልመና መኪናና ድምፅ ማጉያ ስፒከር የሚከራይ አይተናል። እውነት የያዘው በሃሳዊው ጉሮሮው ይዘጋል። አሁን አሁን ከዚህም የባሰ መጥቷል። ዲጂታል የኔ ቢጤዎች ….ጎ-ፈንድ-ሚ-ዎች በዝተዋል። የማህበራዊ መስኮቶች በነዚህ የልመና ጠበብቶች ተሞልተዋል። ‹‹የጉድ አገር ገንፎ እያደር ይፋጃል›› አይደል አባባሉ። ‹‹የምሰራበት የቴሌቪዥን ጣቢያ እንደልቤ ለማናከስ ስላልተመቸኝ በግሌ ዩትዩብ ልሰራ ስላሰብኩ ጎ ፈንድሚ አካውንቴ ላይ ያላችሁን ጣል ጣል አድርጉልኝ›› ይሄ በየዕለቱ የምንሰማው ሃቅ ነው። ጥላቻን ለመዝራት የሰው ኪስ ውስጥ የሚገቡት ስንቶች ናቸው? ክቡር ሕይወት በእርሱ ምክንያት ጠፍቶ በነጋታው የድረ ገፅ ገንዘብ መሰብሰቢያ ከፍቶ በመቶ ሺህ ዶላሮች ይሸቅላል። ይገርማል! ‹‹የእከሌን ብሔር ወክዬ ከእከሌ ጋር እሰጣ አገባ ውስጥ ነው ያለሁት። እኔ እሟገትላችኋለሁ እናንተ ደግሞ ያላችሁን ጣል ጣል አድርጉልኝ›› ይሄ በየደቂቃው በድረ ገፆች የምንሰማው ሃቅ ነው። ከእነዚህ እኩያን የባሰ ግን ሰጪው አብዝቶ ይገርመኛል። ለመልካሙ ጊዜ የማይፈታው እጁ ተዘርግቶ ሳይ ‹‹ምን ነክቶን ይሆን?›› እላለሁ። የስንቱ ህሊናው ታወረ፤ ማስተዋሉ የሰለለ። ለጠብ ደረቱን ነፍቶ፤ በዘመን አመጣሽ አጥር ታጥሮ፤ ሰው ለአጥፊው ይከፍላል። የአንድ ሃሳብ ግዞት ቁራኛ ይሆናል። ያሳዝናል። የተዘረጉ እጆች ሁሉ መልካም ፍሬ የያዙ የሚመስለን ስንቶቻችን ነን? ይገርማል! ለመልካም እጃቸውን የዘረጉ መኖራቸውን አልሳትኩም። ነጠላ ዘርግተው ለምነው ወገናቸውን የሚረዱ ሞልተዋል። እኛ ግን እንዴት እኩዩን ከመልካሙ መለየት አቃተን? ማህበራዊ መስኮት ብዙ እያሳየን ነው። የወገን ድጋፍ የሚሹ መንገድ የወጡ ምስኪን የኔ ቢጤዎች እንዳሉ ሁሉ፤ ሞፈሩን ጥሎ፣ ሥራ ንቆ ልመናንና ማጭበርበርን መርጦ መንገዱን የሞላው እልፍ ነው። እዚህም ሰፈር ያው ነው። ስማቸውን ቀየሩ እንጂ ግብራቸው ግን አንድ ነው። ‹‹ሃሳዊ ዲጂታል ጎ-ፈንድ-ሚዎች›› ዘመናዊ የኢንተርኔቱ ዓለም አጭበርባሪዎች። እንጠንቀቅ!ዳግም ከበደአዲስ ዘመን ግንቦት\n23/2012አዲስ ዘመን ግንቦት\n23/2012", "passage_id": "a8ad4c4b8e8de98cc1f0706682b24568" } ]
959a0341d23c69b534f21b85f895d85a
ab67a66be92828512f05c5478433fd3a
መልሶ ልማት እንዲህም ይካሄዳል
በሀገራችን እየተካሄደ ያለውን መልሶ ልማት ስንመለከት የግል ቤት ላለው ቦታ እና ቤት የመስሪያ ገንዘብ ፤በአስቸኳይ እንዲነሱ ሲፈለግ ደግሞ ለተወሰነ ጊዜ የሚሆን የቤት መከራያ ገንዘብም ይሰጣል።የኪራይ ቤት ውስጥ የሚገኙት ደግሞ ሌላ የኪራይ ቤት ወይም በጋራ መኖሪያ ቤት መንደር ቅድሚያ ክፍያ እንዲፈጽሙ ተደርጎ ቀሪውን በሂደት በሚከፍሉበት ሁኔታ ቤት ይሰጣቸዋል።እስከ አሁን ያለው አካሄድ ይሄው ነው። መልሶ ልማት በኛ ሀገር ብቻ የሚካሄድ ይመስለኝ ነበር። ለካስ ባደጉት ሀገሮችም መልሶ ልማቱ ይሰራበታል።የእነዚህ ሀገሮች አንዳንድ ከተሞች በተደጋጋሚ መልሶ ልማት እንዳካሄዱም የከተማ ልማት ባለሙያዎች ይገልጻሉ።ልዩነት የሚኖረው ልማቱ ሲካሄድ ለተነሺዎች አስፈላጊው ካሳ መስጠቱ ፣መጠለያ ማቅረቡ ላይ ሊሆን ይችላል ።ከዚህ በተረፈ ካሳ ይከፈላል።የመስሪያ ቦታ ይሰጣል። መልሶ ልማት ባደጉት ሀገሮችም ይካሄዳል። የጣልያኗ ሞሊይስ ግዛት አንድ ከተማ መልሶ ልማት ለማካሄድ ማቀዷን በቅርቡ የወጣ የዩፒአይ መረጃ ያመለክታል።ከተማዋ 106 መንደሮች ያሏት ስትሆን ፣ የሁለት ሺ ሰዎች መኖሪያም ናት። ይህችን ከተማ  እንደገና ለመገንባት ሲታሰብም ነዋሪዎቹ የት ሄደው ነው ልማቱ የሚካሄደው የሚለው በሚገባ መላ ተፈልጎለታል። ነዋሪዎቹ ለቤት ኪራይ የሚሆን ብር በየወሩ እየተከፈላቸው ለንግድ ሥራ የሚሆን ገንዘብ ተሰጥቷቸው በጣም ብዙ ሰው በሚኖርባቸው አካባቢዎች በመሄድ የንግድ ሥራ እንዲሰሩ ነው የሚፈለገው። በፈቃደኝነት ለሚነሱ የከተማዋ ነዋሪዎች ይህ የተመቻቸው።ለእነዚህ ተነሺዎች የንግድ እንቅስቃሴ ማካሄጃ ከ27 ሺ ዶላር በላይ እንደሚሰጥ የከተማዋ ባለስልጣናት በቅርቡ ይፋ አድርገዋል። ይህ ብቻም አይደለም ይህን የከተማዋን ራእይ ለማሳካት በፈቃደኝነት ለሚነሱ ነዋሪዎች በወር 770 ዶላር ለሦስት ዓመት ለመስጠትም ተወስኗል ። የመልሶ ልማቱን ሀሳብ ያመነጩት የአካባቢው አማካሪ አንቶኒዮ ቴዴስቺ ‹‹ የከተማዬ ህዳሴ እውን እንዲሆን ፍላጎቱ አለኝ፤የተጎሳቆሉት መንደሮች ታምር የሚታይባቸው እንዲሆኑ እፈልጋለሁ››ሲሉ ተናግረዋል።ይህንንም እውን በማደረግ መሰረታችንን ለመጠበቅ እንሰራለን ሲሉም ለሲኤን ኤን መናገራቸውን ዘገባው አስታውቋል። አማካሪው በመልሶ ማልማቱ በመነሳት ሌላ አካባቢ የሚሄዱ ነዋሪዎችን የመመዝገቡ ሥራ በመጪው መስከረም 16 እንደሚጀመር ጠቅሰው፣ በቅድሚያም ልጆች ያሏቸው ወጣቶት ባለትዳሮች በተፈጠረው እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንደሚደረግም ተጠቁሟል። የመልሶ ልማቱ ግብ በመንደሯ ላይ አዲስ አየር እንዲነፍስ ማድረግና የገጠሩን ኢኮኖሚ ማነቃቃት ነው ያሉት አማካሪው ፣ወደ አካባቢው የሚመጡ ሁሉ በፈለጉት መስክ ኢንቨስት በማድረግ የመንደሯ የፋይናንስ የገቢ ምንጭ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።ሆቴሎች ሬስቶራንቶች ቡና ቤቶች መክፈት ፣አነስተኛ የከተማ ግብርና ማካሄድ ፣የልብስ ቤቶችንና የጌጣጌጥ መደብሮችን ፣ቤተመጻህፍት ሱቆችን መክፈት እንደሚችሉም ጠቁመዋል።አዲስ ዘመን መስከረም 6 / 2012  ዘካርያስ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=18139
[ { "passage": " የሪል እስቴት ቤት አልሚዎች በኢትዮጵያ ከተከሰቱ ሃያ ዓመታት አስቆጥረዋል፡፡ ቁጥራቸውም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ነገር ግን እንደ ብዛታቸው በቤት ጥራት፣ ታማኝነትና ተደራሽነት የሚያደርጉት ፉክክር አልነበረም፡፡ እንደውም ግማሽ/ሙሉ የቤት ዋጋ ተቀብለው የሚሰወሩት ለዓመታት አሳሳቢ ሆኖ ቆይቷል፡፡ አንዳንዶቹም በተባለው ጊዜ ማስረከብ ተስኗቸው ፍርድ ቤት የሚቆሙበት ጊዜም ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ቤት ፈላጊውና አቅርቦቱ ሊመጣጠን አልቻለም፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከቤት ፈላጊዎች ገንዘብ ሰብስቦ ለግንባታ ማዋል ወይም መሰወር ቀርቶ በራሳቸው ወጪ ቤት ገንብተው የሚሸጡ ድርጅቶች እየተፈጠሩ ነው፡፡ ያልገነቡትንም እንደማይሸጡ ማስታወቂያ እያስነገሩ ይገኛሉ፤ መልካም ጅምር፡፡ ከዚህ ተነስተን የመንግስትና የግል ድርጅቶች አመራር ግንባታ፤ የጋራ ማህበረሰብ ግንባታ፤ የኢኮኖሚ ልማት ግንባታና የማህበረሰብ የልቡና ውቅር ግንባታ ---- በኢትዮጵያ በሚገባ ተከውኗል ወይ ብለን እንጠይቅ፡፡ የቤት ግንባታው ከዓመታት በኋላ እንዲሻሻል ተጽዕኖ የፈጠረው የተበዳይ ግለሰቦችን ጩኸት ተከትሎ፣ መንግስት ያወጣው ሕግ ነው፡፡ ሳይገነቡ ገንዘብ መሰብሰብ ተከለከለ፡፡ አልሚዎቹም፤ “ያልገነባነውን አንሸጥም” አሉ፡፡ በሀገሪቱም ለዓመታት ሳይገነባ በቀረ አመራርና አስተዳደር የተነሳ ህዝቦች የተበዳይነት ጩኸት እያሰሙ ነው፡፡ ቆራጥና አፋጣኝ ውሳኔ ማሳለፍ የተሳነው አመራር በመኖሩ፣ በየክልሉ አስተዳደራዊ በደልና ሙስና በማህበረሰቡ ላይ እስከ አፍ ገደፉ እያደረሰ ነው፡፡ አብዛኛው የአስተዳደርና አገልግሎት ሰጪ ተቋም በዕውቀት፣ በዘመናዊ አሰራር ስርአትና በሰብአዊነት (Humanity) ላይ የተገነባ ባለመሆኑ ለችግሩ መባባስ ምክንያት ሆኗል፡፡ አስተዳደራዊ መዋቅሩ ቅንነትን፣ ዕውቀትና ትጋትን መሰረት አድርጎ ባለመቋቋሙ፣የጋራ ማህበረሰባዊ ግንባታው ላይ ተጽዕኖው የጎላ ነው፡፡ በአንድ አካባቢ በሚኖሩ ቅይጥ ማህበረሰቦችም ሆነ ኩታ ገጠም ወረዳዎች መሃህል አለመግባባትና ቅራኔ እንዲፈጠር አድርጎታል፡፡ በዚሁ በቅጡ ባልተደራጀ አመራርና አስተዳደር ሳቢያ፣ የኢኮኖሚ ልማት ግንባታና ስርጭት ውስን ሆኗል፡፡ በአስቸጋሪ ሰዓት ቡጢ ከመጨበጥ ይልቅ የሸሚዝን እጅጌ መሰብሰብና ቃል የተገባውን መፈፀም ተገቢ ነው፡፡ መንግስት በሃቅ፤ “ያልገነባውን አንሸጥም” ማለት አለበት፡፡ ድርጊት እንጂ የሚዲያ ሽፋን ፍትህን፣ እኩልነትና ልማትን አያስገኝምና፡፡ በኢትዮጵያ ከኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግስት አንስቶ አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረስ ዘመናዊ የህዝብ አስተዳደር ትምህርትን ከሰለጠነው ዓለም በመውሰድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየተተገበረ ይገኛል፡፡ ይኸው አስተዳደራዊ (የአመራር) ትምህርት ለፖለቲካዊ፣ ህዝባዊ አገልግሎት፣ መያድና የንግድ ድርጅቶች ተቋማቶቻቸውን እንዴት ለስኬት እንደሚያበቁ የሚያስተምር ነው፡፡ ሆኖም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ እንዳሉት እኩያትና መልካም አገልጋዮች፤(አንደኛው በድግምትና ሰይጣናዊ ስራን በማስፋፋት፤ ሌላኛው እግዚአብሔርን በማገልገልና ቅድስናን በመዝራት እንደሚጠመዱት ሁሉ) የዘመናዊ አመራርና አስተዳደር ተመራቂዎች በሁለት ይከፈላሉ፡፡ አንዱ ወገን ህዝባዊ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ሲደክም፤ ሌላኛው ቡድን ደግሞ ቢሮክራሲያዊ አሰራርን በማስፋፋትና የጥቅም ተጋሪዎችን በጎሳና ሃይማኖት ማዕቀፍ በማደራጀት፣ከሚኖርበት አካባቢ የዘለለ ግንዛቤ የሌለውን ማህበረሰብ መበዝበዝና ሀብት ማካበት ላይ የተጠመደ ነው፡፡ በሀገራችን ዘመናዊ ትምህርት ቢስፋፋም የአመራርና የአስተዳደር አተገባበር ላይ ዘመናዊነት አይታይም፡፡ በየተቋማቱ የሚሰጡ ስልጠናዎች ትኩረታቸው አመራሩን ለማዘመን ሳይሆን የበታች ሰራተኞችን እንዴት መቆጣጠርና ወጪን በመቀነስ በውስን የሰው ኃይል ስራውን ማሰራት ላይ ያተኮረ ነው፡፡ አመራሮች የስራውን ሂደት መረዳትና መምራት ሲገባቸው፤ የተቋማቱ ባላባቶች ሆነው የድርጅቱን ወጪ በስብሰባ አበል፣ ስልጠና እና መሰል እርባና-ቢስ ተግባሮች በማናር፣ የድርጅቱ ገቢ አሽቆልቁሎ በኪሳራ እስከ መዘጋት ያደርሱታል፡፡ የግልም ሆነ መንግስታዊ ተቋማት አመራሮች ለድርጅቱ የገቢ ማሽቆልቆል ተጠያቂ የሚያደርጉት ከጊዜው ጋር የማይሄድ፣ የራሳቸውን አስተዳደራዊ ክህሎትና ደካማ ስነ ምግባር ሳይሆን የፈረደበትን የበታች ሰራተኛ ነው፡፡ ይህ ከህዝብ የተሰጠን ኃላፊነት ለማይገባ ተግባር ማዋልና ተከትሎ ከሚመጣ ተጠያቂነት መሸሽ፣ በተቋሙና ተገልጋዩ ህብረተሰብ መሀል መተማመን ያሳጣል፡፡ በዚህም የተነሳ በማህበረሰቦችና የተቋማት ሰራተኞች ውስጥ የስራ ተነሳሽነትና ምርታማነት እንዳያንሰራራ ዋነኛ ተግዳሮት ሆኗል፡፡ “ምን እውቀትና የሥራ ልምድ አለህ?” ብሎ የሚጠይቅ ሳይሆን “ጎሳህ ምንድነው? የየትኛው ፖለቲካ ወይም ሃይማኖት አባል ነህ?” የሚል ነው መስፈርቱ፡፡ በደርግ ዘመንም ቢሆን ግትር፣ የሰራተኛንና የንግዱን ማህበረሰብ እድገት አንቆ የሚይዝ አመራር ነበር፡፡ አሁን ላይ ደግሞ መዝባሪና ጎሳን መሰረት አድርጎ የተቧደነ አመራር በመሆኑ፣ብሄራዊ ኢኮኖሚና ዜግነት ምኑም አይደሉም፡፡ ይህን ለማረጋገጥ፤ በየክልሉ ባሉ የዞንና ወረዳ አመራርና አስተዳደር አባላት ስለ ዜግነትና የብሔራዊ ኢኮኖሚ ግንባታ ያላቸውን አመለካከት መፈተሸ ነው፡፡ ከደርግ ዘመን የሚሻለው የግል ንግድ እንዲስፋፋ በመፍቀዱ ነው፡፡ በእያንዳንዱ የሙያ ዘርፍ የስነ ምግባር ድንጋጌዎች ቢኖሩም ተግባራዊ ማድረግና አሰራሩም ህግና ደንብን የተከተለ እንዲሆን ክትትል እስካልተደረገበት ድረስ፣ በተቋማት መካከል ያለመቀናጀትና ያለመናበብ ችግር፤ በጥናትና ምርምር የተደገፈ ማሻሻያም ከሌለ፤ የአመራሩና አስተዳደር ድክመት በስንት ጥረትና የገንዘብ ድጋፍ የተቀረፀን የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲ ለሰፊው ህዝብ ጥቅምና የኑሮ መሻሻል እንዳይውል ያደርጋል፡፡ ዘመናዊ ትምህርት በሀገራችን እየተስፋፋ ነገር ግን ዘመናዊ አመራርና አስተዳደርን መተግበር ለምን አቃተን? ጥሩ አባላት ቢኖሩም መልካም አመራሮች በተቋማት ውስጥ ያነሱበት (የሳሱበት) ምክንያት ምን ይሆን? ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ዩኒቲ ዩኒቨርሲ፣ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በአመራርና አስተዳደር ዘርፍ እየተመረቁ የወጡት የአገሪቱን አስተዳደር ስርአት ለምን አላዘመኑትም? በአቶ መለስ ስም የሚቋቋመው የአመራር (Leadership) ማሰልጠኛ ምን ያህል ውጤታማ ይሆናል? ምን አልባት የፖለቲካ ፓርቲ አወቃቀሩ በሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ተጽዕኖ በመፍጠሩ ይሆን? ፖለቲካዊ መዋቅሩ፡- ዕውቀት፣ አስተዳደራዊ ዝንባሌና ትጋትን መሰረት አድርጎ እንደገና ቢሰራ፣በየዘርፉ ያለውን አስተዳደራዊ ችግር እንዲስተካከል ያግዛል? “There is no substitute for character. You can buy brains, but you cannot buy character.” Robert A. Cook", "passage_id": "89102268938fde757a725f3f4d779aab" }, { "passage": "ፀሐይዋ እያዘቀዘቀች ነው፤ የወጣችበትን የምሥራቁን አቅጣጫ ተሰናብታ መጥለቂያዋን ምዕራቡን ይዛለች። በደብዛዛ ፈገግታዋ ልግባ ልቆይ የምትለዋ ፀሐይ መልሳ ትርባለች። በአረንጓዴ ተክሎቹ መሀል በነፋሻማ አየር ታጅቦ ሽው የሚለው አየር ምግብ ነው። አረንጓዴ ከለበሰው መሬት ጋር ተዳምሮ ቦታው ለተመልካች ልዩና ውብ ነው። ማድነቅ ብቻ ሳይሆን በውስጡ አረፍ ማለትንም ይጋብዛል። ይሄ\nስፍራ በመዲናችን አዲስ አበባ ሰሚት አካባቢ ይገኛል። በልዩ መጠሪያው የወጂ ህብረት አምባ አረንጓዴ ቦታ አልሚዎች ማህበር ይባላል። በዚህ ስፍራ ላይ የአካባቢውን ነዋሪዎች ማጣት ፍጹም አይታሰብም፤ የኑሯቸው አንዱ ክፍል አድርገው ጠዋት ማታ በኃላፊነት ይንከባከቡታል። በበጋ የበጋ፣ በክረምት ደግሞ የክረምት ሥራዎችን በመስራት ለአካባቢያቸው ውበት እና ጽዳት ምሳሌ ሆነዋል። በተለይ በዕድሜ ጎልማሳ የሆኑት የአካባቢው ነዋሪዎች በአረንጓዴ ልማት\nቦታ (ግሪን ኤሪያ) ላይ ተሰባስበው የሚመክሩት የአረንጓዴ ቦታቸውን በምን እና እንዴት እንደሚያስውቡት ነው። ጉልበት፣ ጊዜና እውቀታቸውን ሁሉ አካባቢያቸውን ለማሳመር ያውላሉ። ደከመን ሰለቸን ሲሉ አይደመጡም። ሥራውን የሚሰሩት ደግሞ በራሳቸው ተነሳሽነት በኃላፊነት ጭምር በመሆኑ ውጤታማ አድርጓቸዋል። ሌላው ነዋሪም በገንዘብ ፣በሞራል ጭምር ድጋፍ እንደሚያደርጉላቸው የነገሩኝ በማስተባበር ሥራ ላይ የተጠመዱት መምህር ገብረመድህን በሀምላ ናቸው። «የአረንጓዴ ልማት ጥቅሙ ለራስ ነው፤ ሰዎች የድካም ስሜት ሲሰማቸው የአእምሮ መጨናነቅ ሲያጋጥማቸው ሰውነትን ዘና ለማድረግና ንጹህ አየር ለመተንፈስ አረንጓዴና ንጹህ ቦታ ያስፈልጋል። ሕፃናት በንጹህ ቦታ ይጫወታሉ። በየሰፈሩ አረንጓዴ ቦታ ሲኖርና ልጆችም ሆኑ ሌሎች ተገናኝተው መጨዋወት ሲኖር መቀራረብ ይኖራል፤ ይሄም ያፋቅራል። የሰውነት ማጎልመሻ ስፖርት በመስራትም ጤናን መጠበቅ ይቻላል። ለዚህ ደግሞ አረንጓዴ ቦታዎችን ማስዋብና መንከባከብ ያስፈልጋል ።» ይላሉ። አቶ ንጉሴ ክብሩ አስተባባሪ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት አካባቢውን ለነዋሪው  ምቹ በአረንጓዴ ተክሎች ያማረ ከማድረግም በተጨማሪ ሕፃናት እና ወጣቶች የሚያነቡበት ምቹ የማንበቢያ ቦታ ጭምር እንደሚሰራ ይናገራሉ። ይሄ ደግሞ ልጆች አልባሌ ቦታ ላይ እንዳይውሉ ፊታቸውንም ወደ ንባብ እንዲያዞሩ ያደርጋል። ስለዚህ በአካባቢ ሕዝብ እንዲለማና የአካባቢው ሕዝብ እንዲጠቀምበት ነው ያደረግነው። ለተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችም ይውላል። በአሁኑ ሰዓት እየለማ ያለው አረንጓዴ ስፍራ ሦስት ሺ850 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ነው። ካለፉት ዓመታት ጀምሮ እንደ ግራር፣ ወይራ፣ዝግባ … የመሳሰሉትን ሀገር በቀል ዛፎችን ጨምሮ በርካታ ችግኞችን ተክለናል። ቦታውን በብሎኬት በማሳመርና በሳር በመሸፈን ንጹህና ማራኪ አረንጓዴ ስፍራ ለማድረግ እየተሰራ ነው። ለዚህ ደግሞ የአካባቢው ነዋሪዎች ከ500 እስከ 5000 አዋጥተዋል የቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 9 ችግኝ እና ሳር በመስጠት ከፍተኛ ትብብር አድርጎልናል። የቦሌ ክፍለ ከተማ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ቦታውን በአካል በመመልከት እንድናለማ ፈቃድ ሰጥቶናል፤ ውል ወስደናል ሲሉ ነው የተናገሩት። የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዋለልኝ ደሳለኝ እንዳሉት በአዲስ አበባ የሚገኙ የአረንጓዴ ቦታዎችን በደን ከመሸፈን አንፃር በርካታ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ይናገራሉ። ከተማዋን አረንጓዴ የማልበስ ዕቅድ መንግሥት ብቻውን ውጤት የሚያመጣበት ባለመሆኑ ኅብረተሰቡ በተለያዩ አደረጃጀቶች በማህበራት መሳተፍ አለባቸው። በዚሁ መሠረት ሴቶች፣ ወጣቶች፣ የመኖሪያቤት ማህበራት የመሳሰሉት አረንጓዴ ስፍራዎችን ማልማት ላይ ሲሳተፉ ቆይተዋል። አሁን ደግሞ ይበልጥ ተበረታትተው ወደ ሥራው እንዲገቡ ይደረጋል ብለዋል። በክረምቱ ወቅት በችግኝ ተከላ ወደ ሥራ ለሚገቡ ማህበራትም ሆነ ተቋማት አስፈላጊውን ችግኞች እና በጉድጓድ ቁፋሮ እገዛ ይደረጋል። አሁን ከ500ሺ በላይ ችግኞች መኖራቸውን ይገልጻሉ። «የደን ተከላ በአንድ ጊዜ ብቻ የሚሰራ ሥራ አይደለም፤ ዓመቱን በሙሉ የሚሰራ ነው። በመሆኑም ችግኝ ማፍላት፣ ጉድጓድ መቆፈር፣ ከዚያም ችግኝ መትከል ይከተላል። በዚሁ መሠረት ባለፉት አስራ አንድ ወራት ችግኝ የማፍላት ሥራ ተሰርቷል። በተለያዩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች 780 ሺ ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል። ይሄ በራሳችን የተሰሩ ናቸው። እስካሁንም 250ሺ ችግኝ የተተከለ ሲሆን በዚህም ሥራ 19 ሺ ዜጎች ተሳታፊ ሆነዋል» ይላሉ አቶ ዋለልኝ። በቀጣይ እንደ ሀገር አቀፍ ለሚሰራው ሥራም የጉድጓድ ማስቆፈር ሥራ እየተሰራ ነው። አቶ ዋለልኝ እንዳሉት በከተማ አስተዳደሩ በዓመቱ መጀመሪያ የተያዘው ዕቅድ አንድ ሚሊዮን ችግኝ እንተክላለን የሚል ነበር። ሆኖም ግን አሁን ለአረንጓዴ ልማት በተሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የተነሳ ዕቅዱን ወደ ሦስት ሚሊዮን ከፍ በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ነው የገለጹት። ዘንድሮ በሀገር\nአቀፍ ደረጃ አራት\nቢሊዮን ችግኝ ለመትከል\nእቅድ ተይዞ ወደ ተግባር እንቅስቃሴ ተገብቷል።\nሐምሌ 22 ደግሞ በመላ\nሀገሪቱ በአንድ ቀን 200 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል\nታስቧል።አዲስ ዘመን ሀምሌ\n7/2011 በጋዜጣው ሪፖርተር ", "passage_id": "f4b3d0cdbecf0b170f7f9ed5c6fd84fc" }, { "passage": "ኢትዮጵያን ከሞላ\nጎደል\nመግለጽ\nየሚያስችል\nየህዝብ\nትስስር\nይስተዋልበታል።\nየህዝቦች\nየሰላምና\nየመቻቻል\nልኬቱ\nለዘመናት\nበአብሮነት\nየመዝለቅ\nምስጢር\nነው።\nአማራው\nከኦሮሞው፣\nኦሮሞው\nከትግሬው፣\nወላይታው\nከጋሞው፣\nጉራጌው\nከስልጤው\nተጋብተውና\nተዋልደው\nየሚኖሩባት\nየደም\nትስስር\nመመስረቻም\nሆና\nኖራለች፤\nየባሌ\nዞን።\nአቶ\nተስፋዬ\nይልማ\nበጎባ\nከተማ\nየሚገኙ\nየይልማ\nአሞሳ\nሆቴል\nማናጀርና\nባለቤት\nናቸው።\nእርሳቸው\nእንደሚሉት\nሆቴሉ\nበከተማው\nውስጥ\nሆቴል\nባልነበረበት\nወቅት\nጀምሮ\nላለፉት\n60 ዓመታት\nአገልግሎት\nሲሰጥ\nየኖረ\nነው።\nየባሌ\nዞን\nየቱሪስት\nመዳረሻ\nእንደመሆኑም በዚህ አካባቢ ለሚመጣ ቱሪስት አገልግሎት የሚሰጥ ግንባር ቀደም ሆቴል ነው። አሁንም ህብረተሰቡን ከማገልገል ጀምሮ በማህበራዊ ችግሮቻቸው በመድረስ ጭምር ብዙ ማህበራዊ አገልግሎቶችን ሲሰጥ ቆይቷል። ቤተሰቡ በከተማው ተወልደው ያደጉ ከመሆናቸው ሌላ የሚያውቁትም የሚሄዱበትም ሆነ የልማት አጋር የሚሆኑበት አካባቢ ይኖራል ብለው ስላላመኑ በከተማዋ መስራትን እንደመረጡ ተናግረዋል። እርሳቸውም ቢሆኑ እንደሌሎች እህትና ወንድሞቻቸው በውጭ ይኖሩ የነበረ ቢሆንም የአባታቸውን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ ወደ አገር ውስጥ ተመልሰው ቤተሰብንም አገርንም ማገልገል መምረጣቸውን ጠቁመው፤ ሰኔ 23 በተፈጠረው ችግር ስሜት በሚነካ መልኩ ሆቴሉ ሙሉ ለሙሉ መውደሙን ተናግረዋል። እንደ አቶ ተስፋዬ ገለጻ፤ ይህ አስተሳሰብና ተግባር ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚወክል አይደለም። ምክንያቱም ህብረተሰቡ የሚኖረው በሰላምና በፍቅር ነው ። የተወሰኑ ኃይሎች የራሳቸው የሆነ የፖለቲካ ፍላጎት ሊኖራቸው ይችል ይሆናል። የፖለቲካ አስተሳሰብ ግን በዚህ መልኩ ሳይሆን በምርጫ ተወዳድሮ ስርዓት ባለው መንገድ የሚካሄድ እንጂ የተገነባውን ልማት እያፈረሱ የሚገኝ ስልጣን የለም። ከተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጠሩ የጥፋት ድርጊቶች ማንንም አሸናፊ አድርገው የማያሻግሩ፣ የሰውንም ሞራል የሚነኩ፣ ልማቱንም እንደገና ወደታች የሚመልሱና ህብረተሰቡን የሚያቀጭጩ ናቸው ብለዋል። እንደ ይልማ አሞሳ\nሆቴል ሁሉ በሰሞኑ\nበዞኑ ከወደሙ ሆቴሎች\nአንዱ በሮቤ ከተማ የሚገኘው የዘርፌ ግርማይ ሆቴል ነው ፤ ይህ ሆቴል መሰል ጥቃት ሲፈጸምበት በዚህ ዓመት ብቻ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። በሆቴሉ ላይ ስለደረሰው ጥፋት ወጣት መሳይ ዑመር እንዳስረዱት፤ ሆቴሉ በዚህ ዓመት ሲቃጠል ለሁለተኛ ጊዜ ነው። መጀመሪያ ጥቅምት 12 በነበረው ግርግር ተቃጥሎ ነበር። በወቅቱ የወደመው ንብረትም በግምት 11 ሚሊዮን ብር በላይ ይሆናል። በሰዎች እርብርብ በተደረገ እገዛ ከበፊቱ በተሻለ መልኩ ታድሶ ወደ ሥራ ገብቶ ነበር። አሁን ደግሞ ለሁለተኛ ጊዜ ሆቴሉ ሙሉ ለሙሉ በእሳት ወድሟል ይላሉ። ሆቴሉ ከ70 በላይ ሰራተኞች የነበሩት ሲሆን ፤ አሁን ሁሉም ተበትነዋል። ሆኖም የሰው ልጅ ይኖራል፣ ይሞታል በአንድ ግለሰብ ላይ እንዲህ አይነት አስከፊና አጸያፊ ተደጋጋሚ ድርጊት ሲፈጸም ደግሞ መንግሥት ዝም ማለት የለበትም፤ ህብረተሰቡም ሊያወግዘው ይገባል። በመሆኑም መንግሥት አስቸኳይ እርምጃ ወስዶ ለችግሩ መፍትሄ ካልሰጠው ለወደፊቱም ሰርተን ለመኖር ዋስትና የለንም ይላል ወጣት መሳይ። የጎባ ከተማ ነዋሪ አቶ የሺጥላ በድሩ በበኩላቸው፤ በከተማዋ የደረሰው ነገር እጅግ የሚያሳዝን ነው። ተግባሩም ትናንትና በህብረትና በፍቅር አብሮ የኖረውን ህዝብ ነገን አብሮ እንዳይኖር ችግር ለመፍጠር ነው። ለዚህ ደግሞ በማይሆን ትርክት ውስጥ ገብተው ከተለያየ አካባቢ በመምጣት የፈጸሙት ጥፋት ሲሆን፤ በሁከቱ የደረሰው ጉዳት ባለሃብቶችን ብቻ ሳይሆን ህብረተሰቡን ጭምር የሚጎዳ፤ በህዝቦች መካከል መጠራጠርንና ስጋት እንዲፈጠር የሚያደርግ ነው ብለዋል። አቶ የሺጥላ ጉዳት\nየደረሰባቸውም ሆኑ ህብረተሰቡ\nምንም በማያውቀው መልኩ\nውድመት የፈጸሙ ሰዎች\nአላማ ደግሞ አብሮ\nየኖረውን ህዝብ እንዲቃቃር\nየሃይማኖትና የብሄር ግጭት\nውስጥ ገብቶ ወደ\nማያባራ ጦርነት እንዲገባ\nለማድረግ የታቀደ ሴራ\nመሆኑን ጠቁመው፤ አልተሳካላቸውም\nእንጂ ይህንኑ ሞክረው ነበር ይላሉ። እርሳቸው አሁንም መንግሥት በነዚህ አካላት ላይ አስቸኳይ እርምጃ ሊወስድና የህግ የበላይነት ሊከበር ይገባል። ምክንያቱም የህግ የበላይነት የማይከበር ከሆነ ህብረተሰቡ ለአደጋ ይዳረጋል። አሁንም በአካባቢው እየሆነ ያለው ይሄው ሲሆን፤ እነዚህ የጥፋት ኃይሎች ደግሞ ከማዘጋጃ ፣ ከፖሊስና ከሽማግሌዎችም ጭምር በላይ ሆነዋል ብለዋል። አቶ የሺጥላ እያስቸገረ ያለው የጥፋት ኃይል ከየት እንደሚመጣ እንደማይታወቅ ገልጸው፤ ይሄንን የሚያደርጉት ባለፉት 27 ዓመታት ከጥላቻ ስብከት ውጭ ስለፍቅርና አብሮነት እንዲያውቁ ያልተደረጉ ወጣቶች ናቸው። እነዚህ ጥፋተኞችና መመሪያ አቀባዮቻቸው የአካባቢው ማህበረሰብ ትናንትም አብሮ የኖረ ነገም ሳይበታተን አብሮ የሚኖር መሆኑን ማወቅ ይኖርባቸዋል። በመሆኑም መንግሥት በትኩረት መፍትሄ ሊሰጠው፤ ህብረተሰቡም በሰላም እንዳይኖር የሚጥሩ ኃይሎች ላይ እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባ ተናግረዋል። የጎባ ከተማ ከንቲባ አቶ ንጋቱ ሞቱማ በበኩላቸው፤ የተፈጸመው ጥፋት አሳፋሪ ነው። በዚህ ሁነት በከተማው ውስጥ የመኖሪያ ቤቶችንና የንግድ ቤቶችን ጨምሮ 46 ቤቶች ተጎድተዋል። የሁለት ሰው ህይወት ሲያልፍ በአንድ ሰው ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል። በዚህ ተግባር የተጠረጠሩ 56 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል። በቀዳሚነት ደረጃ ሁከቱን ሲያቀናጁ፣ ሲያስተባብሩ፣ ቤንዚን ሲያቀብሉና ቤት እንዲቃጠል አቅጣጫ ያስቀመጡ ብሎም መንገድ እንዲዘጋ ሲያስተባብሩ የነበሩትን ለፍርድ ለማቅረብ በሚደረገው ሂደት እስካሁን ያልተያዙ ስምንት ተጠርጣሪዎች በመኖራቸው፤ እነዚህን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር በማዋል በአጭር ጊዜ ፍርድ እንዲያገኙ ይደረጋል። የተጎዱ ቤተሰቦችን በመደገፍና የወደሙ ንብረቶችን የመተካት ሥራ ከህብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ የሚሰራ ይሆናልም ብለዋል። የሮቤ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱል ጀሊል በበኩላቸው፤ ክስተቱ አስደንጋጭና ከተጠበቀው በላይ ነበር። በሁከቱ በሚያሳፍርም በሚያሳዝንም መልኩ ግለሰቦች ለፍተው ያፈሩትን ንብረት በአንድና በሁለት ሰዓት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ እንዲያጡ አድርጓል። በተፈጠረው ሁከትም ሆቴልና መኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል። እንደ አቶ አብዱል ገለጻ ፤ በግርግሩ አምስት ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ የቆሰሉ ወገኖችም አሉ። የከተማ አስተዳደሩ ኀዘኑን ከመግለጽ ባለፈ ህግ ማስከበርና ተጎጂዎችን የመደገፍ ተግባር ላይ አተኩሮ እየሰራ ይገኛል። እስካሁን 29 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ለህግ ማቅረብ የቻለ ሲሆን፤ ያልተያዙና በቁጥጥር ሥር የዋሉትንም ቢሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለፍርድ እንዲቀርቡ ይደረጋል። አስፈላጊውን ፍርድ እንዲያገኙ እስከመጨረሻው በመከታተል ከስር ከስር እየተሰራም ይገኛል ። እርሳቸው ከዚህ በተጓዳኝ ተጎጂዎች ወድቀው እንዳይቀሩ ህብረተሰቡን በማሳተፍ መልሶ የማቋቋም እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቁመው፤ ተጎጂዎች ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው፣ ኑሯቸውና መደበኛ ሥራቸው እንዲመለሱ ለማስቻል ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል። እንዲሁም ይህን የመሰለ አሳፋሪ ዝርፊያና ቃጠሎ በከተማዋ ዳግም እንዳይከሰት የከተማዋ ነዋሪዎችም ለንብረታቸውም ለህይወታቸውም ዋስትና እንዲኖራቸው፣ በሰላም ወጥተው እንዲገቡ መንግሥት ጥበቃ እንዲያደርግላቸው ከዚህ በፊት የነበሩ ስህተቶችን በማረም ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ወደ ሥራ ለመግባት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 8/2012ወንድወሰን ሽመልስ", "passage_id": "48df7716a58d511e71224b19d9ac66e5" }, { "passage": " በገጠር ገበሬው መኖርያ ቤቱን በእሾህ ያጥራል፡፡ በከተማ ደግሞ አጥር ከማጠር በተጨማሪ ቤት ጠባቂ ውሻ በማሳደግ፣ “ሃይለኛ ውሻ አለ” የሚሉ ማስጠንቀቂያዎች ተለጥፎ ማየት የተለመደ ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን እንዲህ ያለው ማስጠንቀቂያ “አደገኛ አጥር” በሚል እየተተካ የመጣ ይመስላል፡፡ ቀድሞ በጥቂት ግለሰቦችና ድርጅቶች እንዲሁም ኤምባሲዎች ጥቅም ላይ ይውል የነበረው የኤሌክትሪክ አጥር አሁን በብዛት ጥቅም ላይ መዋል ጀምሯል፡፡ “ኔምቴክ”  መቀመጫውን በደቡብ አፍሪካ ያደረገ፣ በ54 የተለያዩ የዓለም አገራት የኤሌክትሪክ አጥር በመስራት የሚታወቅ ዓለምአቀፍ ድርጅት ነው። ሚስተር ዲክ ኢራስመስ፤ በዚህ ድርጅት ውስጥ በኤክስፐርቶች ማናጀርነት ይሰራሉ። በቅርቡ በአዲስ አበባ በኤሌክትሪክ አጥር አተካከልና አጠቃቀም ዙሪያ በተዘጋጀ ስልጠና ላይ የኤሌክትሪክ አጥሮችን ወጪ በሚቆጥብና የላቀ ውጤት በሚያስገኝ ሁኔታ እንዴት መጠቀም  እንደሚቻል አሰልጥነዋል፡፡ ላለፉት 25 ዓመታት በዘርፉ ሲሰራ የቆየው “ኔምቴክ”፤ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ተመሳሳይ ስልጠናዎችን በመስጠት ይታወቃል። በነገራችን ላይ ድርጅቱ ከሚሰራባቸው የዓለም አካባቢዎች አብዛኞቹ የሚገኙት በአፍሪካ ውስጥ ነው፡፡ ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ከወንጀሎች መበራከት ጋር የተያያዘ እንደሆነ ዲክ ኢራስመስ ይናገራሉ፡፡ ኢራስመስ በኤሌክትሪክ አጥር አጠቃቀም ዙሪያ፣ ስለአደገኛነቱና በኢትዮጵያ ስላለው ሁኔታ እንደሚከተለው አስረድተዋል፡፡የኤሌክትሪክ አጥሮች አጠቃቀምየኤሌክትሪክ አጥሮች ውጤታማ እንዲሆኑ ከተፈለገ በመጀመሪያ በደንብ መተከል አለባቸው። የኤሌክትሪክ አጥሮች የሚተከሉት ሰውን ለመግደል አይደለም፡፡ ሌሎች ጉዳቶችንም ማድረስ የለባቸውም፡፡ ደቡብ አፍሪካ በአለም ላይ በርካታ ወንጀሎች ከሚፈፀምባቸው የአለማችን ክፍሎች አንዷ ናት። በአገሪቱ በሚፈፀሙ የተለያዩ ወንጀሎች ብዙ ሰዎች ንብረታቸውንና ህይወታቸውን ያጣሉ። የተለያዩ ወገኖች በኤሌክትሪክ አጥር አስፈላጊነት ላይ ጥያቄዎችን ቢያነሱም በወንጀሎች መበራከት የተነሳ፣ የኤሌክትሪክ አጥር ተጠቃሚዎች ቁጥር በእጅጉ እየጨመረ መጥቷል፡፡ የኤሌክትሪክ አጥር፤ ዝርፊያን ለመከላከልና ደህንነትን ለማረጋገጥ አስተማማኝ ብቃት አለው፡፡ በወጪም አንፃር ቢሆን የተጋነነ አይደለም፡፡ የኤሌክትሪክ አጥርን እኔ “ስሪ ዲ” ነው የምለው። “ዲተር”፣ “ዲቴክት እና “ዲሌይ” ማድረግ ነው ስራው፡፡ በመጀመሪያ አንድ ሰው አጥሩ ላይ ያለውን ማስጠንቀቂያ ሲያይ ወደዚያ እንዳይጠጋ ምልክት ይሰጠዋል፡፡ ያን አልፎ የሰው አጥር መንካት ሲጀምር “ዲቴክት” በማድረግ ገፍትሮ ይጥለዋል፡፡ በዚህም ግለሰቦች ወይም ቡድኖች ሊፈፅሙ ያሰቡትን ወንጀል እንዳይፈፅሙ በማዘግየትና ድምፅ በማሰማት  ሰዎች በንብረታቸው ወይም በህይወታቸው ላይ ሊፈፀም ከታቀደ አደጋ ይጠብቃቸዋል፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን የኤሌክትሪክ አጥሮች በሰው ህይወት ላይ የሞት አደጋ ማድረስ የለባቸውም፡፡ የማይሰሩ የኤሌክትሪክ አጥሮችበመስክ ስልጠናው የታዘብኳቸው ስህተቶች አሉ፡፡ በተለይ የኤሌክትሪክ አጥሮቹ በትክክል አለመተከል ዋነኛው ነው፡፡ አጥሩን ያስተከሉ ሰዎች መስራት አለመስራቱን ስለማያረጋግጡ አጥሩ ቢኖርም ላይሰራ ይችላል፡፡ ዋናው ስህተት በሽቦውና በኤሌክትሪኩ መካከል ያለው ልዩነት ሰፊ መሆኑ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ ወንጀል ለሚፈፅሙ ሰዎች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡  እንዲህ ሲሆን ከኪሳራውም ባሻገር ሰዎች ለዘረፋና በህይወት ላይ ለሚቃጣ አደጋ ይጋለጣሉ፡፡ ሌላው አጥሩ ላይ ሌሎች ነገሮች ተሰቅለው የሚታዩበት ሁኔታ መኖሩ ነው፡፡ የሆኑ ብረቶች ተቀላቅለው ያየሁባቸው ቦታዎች አሉ፡፡ ዛፍና አትክልቶች ከአጥሩ ጋር ይቀላቀላሉ፡፡ እነዚህ ነገሮች የኤሌክትሪክ አጥሩ በተገቢው መንገድ አገልግሎት እንዳይሰጥ እንቅፋት ይሆናሉ፡፡ በስልጠናው ወቅት የኤሌክትሪክ አጥር የሚተክሉ ሰዎች በተገቢው መንገድ እንዲተክሉ በንድፈ ሃሳብና በተግባር የታገዘ ስልጠና ሰጥተናቸዋል፡፡ ከቤት ውበት ጋር በተያያዘም አተካከሉ ላይ የሚደረጉ ጥንቃቄዎች ተዳስሰዋል፡፡ አጥሩን ሊነካ የሚሞክር ሁሉ ወንጀለኛ ነው ብሎ ለመደምደም አስቸጋሪ ስለሚሆን፣ ይህ አጥር በተተከለበት ቦታ ሁሉ በግልፅ ሥፍራ የማስጠንቀቂያ ማስታወቂያ መለጠፍ ግዴታ ነው። ይሄ በደቡብ አፍሪካ በህግ ተደንግጐ የተቀመጠ ጉዳይ ነው፡፡ ይህንን አጥር የሚተክሉ ሰዎች ተገቢ ስልጠና ያገኙ መሆን እንዳለባቸው ህጉ ይደነግጋል፡፡ ባለቤቱ ሰው የማይገድልና የጥራት ደረጃውን ያሟላ ምርት መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለበት ተቀምጧል፡፡ ማስጠንቀቂያውን ያላዩ ሰዎች አጥሩን ቢነኩ እንኳን ገፍትሮ ይጥላቸዋል እንጂ አይገድላቸውም፡፡  በዚህ አጥር እንስሳትም ቢሆኑ መጐዳት የለባቸውም፡፡ በኤሌክትሪክ አጥሩ ጉዳት የሚደርስባቸው በማንኛውም ኤሌክትሪክ ሊጎዱ የሚችሉ እንደ  ሸረሪትና እባብ አይነት እንስሶች ብቻ ናቸው፡፡ ወፎች የሚቆሙት  ብረቶቹ ላይ ስለሆነ ጉዳት አይደርስባቸውም፡፡ አፍሪካ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በብዙ ቦታዎች እንደ ስዊድን፣ አውስትራሊያና ኔዘርላንድስ ባሉ አገራትም የኤሌክትሪክ አጥሮች ብዙ ህይወቶችንና የንብረት ጉዳቶችን ታድገዋል፡፡ አጥሮቹ መብራት በሌለበት ጊዜ የባትሪ መጠባበቂያ ስላላቸው ስራቸውን አያቋርጡም፡፡ እኔ እንዳየሁትና ከሌሎች ቦታዎች ጋር እንዳነፃፀርኩት፣  አዲስ አበባ ያለው የመብራት ሀይል አቅርቦት እምብዛም የከፋ አይደለም፡፡ ኬኒያ፣ ናይጄሪያና፣ ጋና በመሳሰሉት አገራት የሀይል አቅርቦቱ እጅግ አስቸጋሪ ነው፡፡ ተከታታይ የሀይል አቅርቦት በማይኖርባቸው ጊዜያት ወይም ቦታዎች ሶላር እንጠቀማለን፡፡ አዲሱ የ“ደህንነት” ኩባንያአቶ ሳምሶን ገብረስላሴ፤ የ“ሳሜክ ኢንጂነሪንግ” ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ በቅርቡ በ ደህንነት እና አደጋ መከላከል ስራ ላይ የተሰማራ አዲስ ድርጅት በአዲስ አበባ ከፍተዋል፡፡  “ሳሜክ ኢንጂነሪንግ ለንደን የሚገኘው የ “ሳሜክ” ኩባንያ እህት ድርጅት ነው፡፡ የደህንነት እና የአደጋ መከላከያ እቃዎችን ከውጪ በማስመጣት፣ በኢትዮጵያ በዚህ ስራ ላይ ለተሰማሩ ድርጅቶች ያቀርባል፡፡ እነዚህ ድርጅቶቹ መሳሪያዎቹን ከመግጠማቸው በፊት ስልጠናዎች በመስጠት ጥራቱን የጠበቀ ሥራ እንዲሰሩ ያግዛል፡፡ የ“ኔምቴክ” ስልጠናም የዚሁ አካል ነው፡፡ የ“ሳሜክ ኢንጂነሪንግ” ባለቤት አቶ ሳምሶን ገ/ሥላሴ፤ በኢትዮጵያ ስላለው የኤሌክትሪክ አጥሮች ተሞክሮአቸውን እንዲህ ይገልፁታል፡፡ “እኛ አገር ያለው ችግር አጥሩ  በብዛት የሚተከለው በልምድ ነው፡፡ ከዚህ በፊት የሚጠቀሙት ኤምባሲዎችና ትልልቅ መስሪያ ቤቶች ነበሩ፤ አሁን ግን ወንጀል እየተበራከተ ሲመጣ በመኖሪያ ቤቶች በስፋት እየተገጠመ ነው፡፡ አጥሩ መስራት አለመስራቱ የሚታወቀው ሌባ ያን አጥር ነክቶ ገፍትሮ ሲጥለው ነው፤ ተከላው በትክክል ስለማይከናወን ውጤታማነቱ አጠያያቂ ነበር። የሚገጥሙት ሠራተኞች መስራት አለመስራቱን ለማወቅ በቂ ስልጠናም ሆነ ማረጋገጫ መሳሪያዎች አልነበራቸውም፡፡ ከዚህ በፊት የተገጠሙትን ስናይ፤ መስመሩ የተላቀቀ፣ የተቆራረጠ፣ በቂ የኤሌክትሪክ ሀይል የሌለው ሁሉ አጋጥሞናል፡፡ ወደፊት ተከታታይ ስልጠናዎች ይኖራሉ፤ የሚተክሉት ሰዎች ብቃት ያላቸው እንዲሆኑና በአገራችን መንግስት የኤሌክትሪክ አጥር ህግ እንዲያወጣ ግፊት እናደርጋለን፡፡”እስከዚያው ግን የኤሌክትሪክ አጥር ባለበት ሥፍራ ሁሉ ይሄንኑ የሚገልጽ ማስታወቂያ በግልፅ በሚታይ ቦታ ላይ መሰቀል እንዳለበት ባለሙያዎቹ በአጽንኦት ይናገራሉ፡፡", "passage_id": "dd0e0f9cece73304bffe96b4a3e36316" }, { "passage": "ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ቦታው ስንዴና ጤፍን ጨምሮ የተለያዩ የጥራጥሬ እህሎች ይመረትበት ነበር። በ2003 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦታውን ከተረከበ በኋላ እስከ 2008 ዓ.ም መጨረሻ ለደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃነት ሲጠቀምበት ቆየ። ሆኖም በቦታው የሚጣለው ቆሻሻ ውሎ እያደር በአካባቢው አርሶ አደሮችና በቤት እንስሳዎቻቸው ላይ የጤና ጉዳት እያስከተለ መጣ። ከቦታው ለተፈናቀሉ አርሶ አደሮች የተከፈለው የካሳ ክፍያም በቂ ባለመሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግር ፈጠረ። ይህንንም ተከትሎ በአካባቢው በተፈጠረ ተቃውሞ በቆሻሻ ማስወገጃ ቦታው የሚገኙ ቢሮዎች፣ መጋዘኖችና ጋራዦች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮም ቦታው ቆሻሻ እንደወረሰው፤ የአርሶ አደሮቹም ጥያቄ ሳይመለስ ለዓመታት ቆይቷል። ዛሬ ላይ ግን በፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን በረክ ወረዳ ከቦታው ለተነሱና የእርሻ ማሳቸው በከፊል ለተወሰደባቸው አርሶ አደሮች የሰጠው ምላሽ ለጊዜውም ቢሆን እፎይታን የሰጠ ይመስላል። አርሶ አደር ፀጋዬ ዘውዴ በበረክ ወረዳ ሀብሩ ቀኖ ኩራጊዳ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነዋሪ ናቸው። ቀደም ሲል በለም ማሳቸው ስንዴ፣ጤፍ፣ጓያ፣ባቄላና ሽምብራ ያመርቱ ነበር። ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ለቆሻሻ ማስወገጃ የከተማ አስተዳደሩ አነስተኛ ካሳ ከፍሏቸው ሁለት ሄክታር የእርሻ ቦታ እንደተወሰደባቸው አርሶ አደሩ ይናገራሉ። ይህንንም ተከትሎ ምርታቸው መቀነሱንና እህል ሸጠው የሚያገኙት ገቢም አነስተኛ እንደነበር ያስረዳሉ። የተወሰደባቸውን መሬት ለማስመለስ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን ለዓመታት ሲታገሉ መቆየታቸውንም ጠቅሰው፤ በቦታው ላይ በተጣለው ቆሻሻ ምክንያት በቤተሰባቸውና ቤት እንስሳዎቻቸው ላይ የጤና ጉዳት ሲደርስ እንደቆይም ይናገራሉ። በሀገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን በረክ ወረዳ አስተዳደር ከዞኑና ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመነጋገር ቆሻሻ ከተደፋበት ውጪ ያለውን መሬት ከሌሎች አርሶአደሮች ጋር በጋራ እንዲያለሙ በመፍቀዱ መደሰታቸውን ይገልፃሉ። በወረዳ አስተዳደሩ በኩል አሁን ለአርሶአደሩ የተሰጠው ምላሽ ከፊል በመሆኑ በቀጣይ በቆሻሻ መጠያው ስፍራ ያሉት ለቢሮ አገልግሎት የሚሰጡ ህንፃዎችና፣ የመኪና ማቆሚያ መጋዘኖች እንዲሁም ቆሻሻው የተጣለባቸው አካባቢዎች ለአርሶ አደሩ መልሰው ጥቅም እንዲሰጡ የወረዳው አስተዳደር ሊሰራ እንደሚገባም አቶ ፀጋዬ ያመለክታሉ። አርሶ አደር ነገሰ መገርሳ በበረክ ወረዳ አቃቂ ቂሌ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነዋሪ ናቸው። በ2003 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቆሻሻ መድፊያ በሚል በአነስተኛ ካሳ ክፍያ 5 ሄክታር መሬት እንደተወሰደባቸው ያስረዳሉ። በወቅቱ እርሳቸውና ሌሎች አርሶ አደሮች በማሳቸው ላይ በሄክታር 100 ኩንታል ስንዴ ሲያመርቱ እንነደነበር አስታውሰው፣ በዚሁ ልክ ካሳ እንዲከፈላቸው ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ያስታውሳሉ። ይሁንና ማምረት የምትችሉት በሄክታር 50 ኩንታል ነው በሚል ስሌት የካሳ ክፍያው እንደተሰጣቸውና በጊዜው እርሳቸውና ሌሎች አርሶ አደሮች ተገቢ ባልሆነ ከካሳ ከማሳቸው ላይ በመፈናቀላቸው በርካታ ችግሮች ሲገጥማቸው እንደቆዩ ይናገራሉ። በተለይ ማሳቸውን ሙሉ በሙሉ ያጡ አርሶ አደሮች ለከፋ ድህነት ተጋልጠው መቆየታቸውንም ያስረዳሉ። የቆሻሻ መጣያው ወደ ስራ ሲገባ ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያ፣ መንገድ፣ ውሃና መብራት እንደሚሰራላቸውና የስራ እድልም እንደሚፈጠርላቸው በከተማ አስተዳደሩ በኩል ቃል ተግብቶላቸው እንደነበርም አርሶ አደሩ አስታውሰው፤ ይህ ሁሉ እንዳልተሰራላቸውና በወቅቱ ስለቆሻሻ ማስወገጃው ዝርዝር መረጃም ለማወቅ ተቸግረው እንደነበር ይገልፃሉ። አቤቱታቸውን ለሚመለከታቸው አካላት በተደጋጋሚ ቢያቀርቡም በቂ ምላሽ ሳያገኙ ለዓመታት እንደቆዩና ከሁለት ዓመት ወዲህ በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ተወስዶባቸው የነበረውን የእርሻ መሬት ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በጋራ በማረስ እንዲጠቀሙ የወረዳው አስተዳደር እንደፈቀደላቸው ይናገራሉ። በቀጣይም ቆሻሻ መጣያው ያረፈበት ቦታ ከቦታው ለተፈናቀሉ አርሶ አደሮች ዳግም ጥቅም እንዲሰጥ የወረዳ አስተዳደሩን ምላሽ እንደሚጠይቅም ያመለክታሉ። በፊንፌኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የበረክ ወረዳ አስተዳደር ምክትል አስተዳደር አቶ ምትኩ ለሜሳ በበኩላቸው እንደሚገልፁት፤226 ከሚሆኑ አርሶ አደሮች በቂ ካሳ ሳይከፈል ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃነት ሲውል የነበረው 165 ሄክታር ቦታ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ ቆይቷል። በተለይ ደግሞ በቦታው ላይ ሲጣል የነበረው ቆሻሻ በአካባቢው ባሉ አርሶ አደሮችና የቤት እንስሳዎቻቸው ጤንነት ላይ ጉዳት ሲያስከትል ነበር። መንግስት ባወጣው አቅጣጫ መሰረት ያለበቂ ካሳ ክፍያ መሬት የተወሰደባቸው የአካባቢው አርሶ አደሮች 65 ሄክታር መሬት ቆሻሻ የተጣለበት ስፍራ መፍትሄ እስኪያገኝ ድረስ መታረስ የሚችለውን 100 ሄክታር መሬት በጋራ እንዲያርሱትና ከምርቱ እኩል እንዲጠቀሙበት የወረዳ አስተዳደሩ ወስኗል ይላሉ። ለዚህም ከአርሶ አደሮቹ የተውጣጡ ሰዎች ያሉበት ኮሚቴ ተዋቅሮ እርሻውን አሁኑኑ እንደሚጀምሩ ጠቅሰው.፣ የወረዳ አስተዳደሩ ጉዳዩ አስካሁን መቆየቱ ተገቢ አለመሆኑን በመገንዘብ አርሶ አደሩ በመሬቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ከልዩ ዞኑ ጋር በመሆንና ወደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ በመሄድ ጉዳዩ እንዲፈታ ጥረት ማድረጉን ያመለክታሉ። እንደ ምክትል አስተዳደሪው ገለፃ፤ ቆሻሻ የተጣለበትን ቦታና የማስወገጃ ጣቢያው ያረፈበትን ቦታም በተመሳሳይ ከቦታው ለተነሱ አርሶ አደሮች ተመልሶ ጥቅም እንዲሰጥ ለማድረግ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር ድርድር ለማካሄድ ኮሚቴ ተቋቁሟል። የአርሶ አደሮቹ ጥያቄ በከፊል የተመለሰ ቢሆንም፣ ቆሻሻ የተጣለበት ቦታ፣ ቢሮና መጋዘን ያረፈበት የመሬቱ ክፍል ጉዳይ ገና መፍትሄ ያላገኘ በመሆኑ በቀጣይ ለአርሶ አደሮቹ በቂ ካሳ ከፍሎ ለከተማ አስተዳደሩ በቶሎ ቦታውን ለማስረከብ አልያም ደግሞ ቦታው ተመልሶ ለአርሶ አደሮቹ ተሰጥቶ በማህበር ተደራጅተው እንዲያለሙበት ይደረጋል። አዲስ ዘመን ሰኔ 9/2012 አስናቀ ፀጋዬ", "passage_id": "b002f788ea9865896b9489b60ec67b9e" } ]
61f74052e7e32095b1bf9f1e04297c2c
16afee1fe8a5999fb9695d091aca4876
መንታ ልጆቿን ለእዳ መክፈያ እና ሞባይል መግዣ
በሀገራችን ወልዶ መሳም ብዙ ትርጉም አለው። ልጅ ሲወለድ ያለው ደስታም ከዚህ ሁሉ የመነጨ ነው።ልጅ መውለድ ዘር መቀጠሉን ማረጋገጥ ከመሆኑም በተጨማሪ ትዳርን ለማጽናት ወሳኝ እንደሆነም ይገለጻል። እናት የምትከበረውም አንድም ሕይወት በመስጠቷ ነው። እናቶችም ልጆቻቸውን በማጥባት እና የተለያዩ እንክብካቤዎችን በማድረግ ለቁምነገር ያበቃሉ። ከልጅ በላይ ምንም ነገር እንደሌለም በማመን ብዙ ጥቅሞቻቸውን እስከ ማጣት ይደርሳሉ። ሰሞኑን ከወደ ቻይና የወጣ መረጃ እንዳመለከ ተው ግን የልጅ ጉዳይ ብዙም ቁብ ያልሰጣት አንዲት እናት መንታ ልጆቿን መሳም ፣አሳድጎ ለቁም ነገር ማብቃት አልፈለገችም። ልጆቿን ስትል መጎዳትም  አልፈለገችም። ከዚህ ሁሉ ይልቅ የወለደቻቸውን መንታ እምቦቀቅላዎች በ65ሺ የን ማለትም በ9ሺ 100 ዶላር ትሸጣቸዋለች። ይህን በማድረጓም ተደርሶባት በፖሊስ በቁጥጥር ሥር ውላለች። ስሟ ያልተጠቀሰው ይህች ቻይናዊት መንታ ልጆቿን የሸጠችው እንደተራራ እየወለደና እየተከመረ ያለውን ዕዳዋን ለመክፈል እንዲሁም አዲስ ዘመናዊ የኪስ ስልክ ለመግዛት አስባ ነው። ኒኝቦ ኢኒንግ ኒውስ የተባለው የቻይና ጋዜጣ ዕድሜዎቿ በ20ዎቹ እድሜ ውስጥ የምትገኘው ይህች እናት መንትያ ህጸናቱን የሸጠቻቸው የዛሬ ዓመት ነው።ለመሸጥ ስታስማም የተጠቀመችባቸው ምክንያት በችልተኛነት መጠቃቷንና በዕዳ ውስጥ መዘፈቋን ነው ብሏል። በቅፅል ስሟ ማ የምትባለው ይህቺ ልበደንዳና እናት እንደተናገረችው ቤተሰቦቿ በቅድመ ጋብቻ ከተከሰተው እርግዝና ጀምሮ ሲናደዱና ሲንገበገቡ ቆይተዋል። በዚህ የተነሳም እርሷን ለመርዳትና ሕጻናቱን ለማሳደግ አልፈቀዱም። ዉ በመባል ብቻ የሚታወቀው የልጆቹ አባት ከህጻናቱ ጋር ምንም ነገር ማድረግ እንደማይፈልግ ግልፅ አድርጎላታል። የመንትያዎቹ እናት የአንድ ወር ዕድሜ ላላቸው መንትያ ልጆቿ ገዢዎችን ማግኘት እንዳልተቸገረች ገልጻለች። ፖሊስ ይህን አስደንጋጭ የጨቅላ ህጻናት ሽያጭ መረዳት የቻለው አንድ ተመሳሳይ አስደንጋጭ የህጻናት የሽያጭ ሁኔታዎች ፍንጭ ማየቱንና ምርመራም እያደረገ መሆኑን ነው። ፖሊሶች ጥልቅ ምርመራ ካደረጉ በኋላ ህጻናቱ በአንሁይ ግዛት ለሁለት የተለያዩ ጥንዶች መሸጣቸውን ደርሰውበታል። አንደኛው በፉያንግ ሌላኛው ደግሞ በሱዦይ ማለት ነው ሲል ፓሊስ አብራርቷል። ምንም ዓይነት ነገር ማድረግ ያልፈለገው ድምፁን አጠፍቶ የነበረው የህጻናቶቹ አባት ተቆርቋሪ መስሎና ለምን በሚል የአንደኛውን ህጻን ድርሻ ለመካፈል ከተሸጡ በኋላ መታየቱ ተጠቁሟል። እናትየው ለፖሊስ እንደተናገረችው ሕጻናቱን የሸጠችበትን ገንዘብ ለልጆቿ አባትም አካፍላለች። የራሱዋን ድርሻ የባንክ ዕዳዋን ለመክፈል እና አዲስ ስማርትፎን ለመግዛት የተጠቀመችበት ሲሆን፣ ዉ ደግሞ የቁማር ዕዳዎቹን ይወጣበታል እየተባለ ነው። ፖሊስ ህጻናቱን ለማግኘት በአንሁይ በመረባረብ ላይ ሲሆን፣ ከማ ወላጆች ዘንድ ለማኖርም ፈልጓል። በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ ኃላፊነት የማይሰማቸው ወላጆች ፅኑ የእስራት ጊዜ ይጠብቃቸዋል። በተያዙ ጊዜ ለፈጸሙት የማይገባ ተግባርም የሸጡት ገንዘብም እነሱም በቁጥጥር ሥር ይውላሉ።አዲስ ዘመን መስከረም 6 / 2012  በኃይለማርያም ወንድሙ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=18142
[ { "passage": "‹‹ማዕድን›› ማጋራት የርህራሄነት ሀብታምነት እንጂ የቁስ ባለፀጋነት ጉዳይ አለመሆኑን ተረድቻለሁ። በወረርሽኙ ጦስ ምክንያት ገቢያቸው የነጠፈባቸውና ተንጠፍጥፎ የዕለት ጉርስ የቀራቸው ወገኖች ጭምር የማዕድን ማጋራት ዘመቻ መቀላቀላቸው የትርፍ ጉዳይ እንዳልሆነ ከቋንቋም በላይ ነው። የስሜት፣ የሐሳብ አንድነት፣ የልብ መውደድ ጉዳይ ነው፤ ወገንን ከስቃይ ማዶ አሻግሮ ነገን የማየት ተስፋ። በዚህ ሰዓት የዚህ ዘመቻ አካል የሆናችሁ ኢትዮጵያውያን ለእናት አገር ጥሪ ምላሽ በመስጠታቸው ሊመሰገኑ እንደሚገባ ድጋፍ የተደረገላቸው አካላት ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም ዜጎች ይናገራሉ። \nየማዕድ ማጋራቱ ጉዳይ ዓላማን የመጋራት ጉዳይ፣ ብሶትን የመካፈል ጉዳይ፣ ራባቸውን የማስታገስ ጉዳይ እንጂ የፖለቲካ ስሌት አይደለም። ለወገን ርሃብና ችግር መድረስ ፖለቲከኝነት ከሆነም እሰየው። የማዕድ ማጋራት ጉዳይ አብሮ አረንቋውን የመሻገር ጉዳይ፣ ከውሃ ሙላት የማሻገር ጉዳይ እንጂ የትርፍ መወርወር ጉዳይ አይደለም። \nየወረርሽኙ ብትር ቀጥሏል። የማዕድ ማጋራቱም ጉዳይ እንዲሁ። የሕጻናትን ልብ የሚያንጠለጥል ለቅሶ ላለመስማት፣ የእናትን ልብ የሚሰብር ትካዜ ላለማየት ገንዘብ መታደልን ሳይሆን ቅን ልብ መታደልን እንደሚጠይቅ አሳይተውናል። ዛሬ የዚህ ዓይነት ታሪክ ተቋዳሾችን የቅን ልብ ባለቤቶች ‹‹እኔም ስለወንድም እና እህቶቼ ያገባኛል›› የሚል ቅን ምላሽና እጃቸውን ለወገኖቻቸው ስለዘረጉ የህጻናት ማሳደጊያ ልጆች አወጋችኋለሁ። \nነገሩ እንዲህ ነው። ወላጅ አልባነት በአንድ እንዲከትሙ አድርጓቸዋል። መወለድ ሳይሆን መዋደድ እህትና ወንድም አድርጓቸዋል። ፍቅርን፣ አንድነትን፣ መዋደድን፣ መከባበርን ሲሰበኩ አድገዋል። የራሳቸውን አሳዳጊና ተንከባካቢ እናት፣ የሌሎችን ተንከባካቢ አክስት፣ እህል ውሃ ያሰባሰባቸውን እኩዮቻቸውን እህትና ወንድም፣ የጧት ጠያቂና ፈቃጃቸውን አባት አድርገው አድገዋል፤ ከ14 ዓመታት በላይ አብረው ኖረዋል። \nበዚህ ሁኔታ ያደጉት የኤስ ኦኤስ ልጆች መልካ ምነትና ደግነትን ከኢትዮጵያዊነታቸው ባሻገር በደግነት ከወለዷቸው ከአባታቸው ከፕሮፌሰር ሃርማን ግማይነር እና ማዕድ ማጋራትን ሰው የመሆንን አንድ ሚዛን ከሚያስቀድሙት ጠቅላይ ሚንስትራቸው ዶክተር አብይ አህመድ በመውረስ ‹‹በመተባበር፣ በመደጋገፍ ይሄን አስቸጋሪ ወቅት እናልፈዋለን›› በሚል ከየተበተኑበትና ከያሉበት የተለያየ የዓለም ክፍል በአላማ ጽናት ባሰባሰባቸው ‹‹የኤስ ኦ ኤስ የቀድሞ ልጆች ማህበር በኢትዮጵያ›› አማካኝነት ያሰባሰቡትን 120 ሺህ ብር የተለያዩ የዕለት መጠቀሚያ ቁሳቁሶች (ዘይት፣ ሩዝ፣ መኮሮኒ፣ ሳሙና፣ ፓስታና ዱቄት) በመግዛት ለ77 አቅመ ደካማ ወገኖቻቸው ለአንድ ወር ቢሆናቸው ሲሉ በዕለተ ሰንበት ግንቦት 23 በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 አስረክበዋል። በሕጻናት መንደር ሰው መሆንና መዋደድን ለምደው ማደጋቸው የሕጻናት ብሶትና የእናቶች መቸገር ከስጋቸው ዘልቆ አጥንታቸውን ይሰረስራቸዋል። መተጋገዝ ለአቅመ ሀብታም መድረስን አይጠይቅም ባይ ናቸው። ከአንደበታችሁ ከልባችሁ ስሙ። \nየማህበሩ ሊቀመንበር አቶ እዮብ በቀለ እንደተናገሩት፣ በመላው ዓለምም ሆነ በኢትዮጵያ በተከሰተው የኮቪዲ 19 ወረርሽኝ ምክንያት በርካታ ወገኖች ከሥራ ተለያይተዋል። በዚህ የተነሳም ሥራ ሠርተው ራሳቸውንና ልጆቻቸውን መግበው ማደር እየተቸገሩ ይገኛሉ። በመሆኑም ‹‹ወገኖቻችንን እና እህቶቻችንን ለማሰብ›› የተገናኙበት ፕሮግራም እንደሆነ ይገልፃሉ። ‹‹የወገኖቻችን ችግር የእኛ ችግር ነው፣ ሲርባቸው ይርበናል፤ ሲጠማቸው ይጠማናል›› ሲሉ ክፉ ጊዜን እጅ ለእጅ ተያይዘን እንሻገር። ለስጦታ ቅንነት እንጂ ሀብት አይወስነውም፤ ያለንን በመስጠት ለወገኖቻችን የምንደርስበት፣ ሰው የመሆናችን ሚዛን የሚሰፈርት፣ አዛኝ ልብ እንዳለን የምንታይበት፣ ያለንን በማካፈል ታላቅነትን የምንጎናፀፍበት ጊዜ በመሆኑ ወገኖቻችንን ልንደርስላቸው ይገባናል ሲሉ ጥሪቸውን አስተላልፈዋል። ለዚህ የተቀደሰ ተግባር በአጭር ጊዜ 120 ሺህ ብር በማበርከት እጃቸውን የዘረጉ የማሳደጊያ እህት ወንድሞቻቸውን በማመስገን ድጋፋቸው የወገኖቻችን ችግር እስኪቃለል ድረስ እንዲቀጥል ተማጽነዋል። \nየማህበሩ አባል የሆነው አቶ ሃይለሚካኤል ዋስይሁን እንደተናገሩት በኤስ ኦ ኤስ ሕጻናት ማሳደጊያ ክፉ ደጉውን ተምረው በማሳለፍ ራሳቸውን ችለው የሚኖሩ እህት ወንድሞቻቸው ጋር በእንዲህ ዓይነት ደግ የማዕድ ማጋራት ተግባር በመገናኘታቸው አመስግነዋል። በማህበራዊ ሚዲያ ጥሪ ከያሉበት ቀና ምላሽ የሰጡትን የማህበሩ አባላት እሰየው ድጋፋችሁ ለወገናችሁ ደርሷል ብለዋል። ማህበራዊ ሚዲያን ለሰብዓዊነት ተግባር እንጂ ለአረመኔነት ተግባር አታውሉ፤ ለወገን ለመድረስ ሰውነትን እንጂ ሀብታምነትን አትጠብቁ ሲሉ ከሕጻናት መንደር አድገው ለሕጻናት ችግር ለመድረስ ከሚጥሩት ልምድ እንዲቀስሙ መክረዋል። \nበአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የወረዳ 12 ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሸለመ ታደሰ በበኩላቸው እነዚህ ተስፋ ያላቸው ወጣቶች የወቅቱ ችግር በወገናቸው ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ አሳስቧቸው የአቅማቸውን በማበርከታቸው ምስጋና ችረዋል። ከእነዚህ ወጣቶች በጎ ተግባር ሌሎች የሚማሯቸው በርካታ ቁም ነገሮች አሉ። በወረዳው ከሰባት ሺህ 730 በላይ ነዋሪዎች በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ እንደሚገኙ ተለይተው የወገናቸውን ድጋፍ የሚሹበት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። ስለዚህ በወረዳው በሰባት ቀጠናዎች በተዘጋጁ መጋዘኖች ወጣቶች፣ ባለሀብቶች፣ አርሶ አደሮች እና አጠቃላይ ሕብረተሰቡ የአቅሙን በማበርከት ላይ መሆኑን በመግለጽ አመስግነዋል። \nአቶ ሸለመ እንዳሉት፤ ከዚህ የባሰ ጊዜ የሚመጣ ከሆነ ወገኖቻችን ለከፋ ጉዳት እንዳይጋለጡ ድጋፋችንን አጠናክረን ልንቀጥል ይገባል። በእንዲህ አይነት ቅንነትና ርህራሄ የተሞላበት ተግባር ሰው የሆነ ሁሉ እንዲሳተፍ በወረዳው ስም ጥሪያቸውን አስተላፈዋል። በመጨረሻም ‹‹በሕክምና ባለሙያዎቻችንና በመንግሥታችን በኩል የሚተላለፉ መልዕክቶችን ሳይዛነፉ በመተግበር ከወረርሽኙ ራሳችንን፣ ቤተሰቦቻችንን እና ወገኖቻችንን ልንጠብቅ ይገባል።አዲስ ዘመን ሰኔ 5/2012ሙሐመድ ሁሴን", "passage_id": "854583c935b760e3ee8e0d0f86c2e20c" }, { "passage": "ባለፉት 30 ዓመታት ለ\n7 ሺ 800 ህጻናት በነጻ የልብ ቀዶ ህክምና አገልግሎት ሰጥቷል። ይህ በዓለም ላይ ትንሽ ገንዘብ ነው የሚጠይቁት በሚባሉ ሆስፒታሎች ሂሳብ እንኳ ቢሰራ ከ 3 ነጥብ\n5 ቢሊየን ብር በላይ የሚያወጣ አገልግሎትን ለኢትዮጵያውያን የሰጠ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ። ተማሪ\nቤተልሔም ታምሩ የልብ ህመም እንዳለባት የታወቀው ገና በህጻንነቷ ነው። ተወልዳ ባደገችበት አዳማ እንዲሁም አዲስ አበባ እየመጣችም ለአስር ዓመት ያህል ያለማቋረጥ ህክምናን አድርጋለች። በነዚህ ሁሉ ዓመታት ደግሞ ለቀዶ ህክምና ወረፋ እየጠበቀች ነው የቆየችው። ቤተልሄም የቀዶ ህክምናውን ያገኘችው ከአራት ዓመት እልህ አስጨራሽ ጥበቃ በኋላ በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ውስጥም ቀዶ ህክምናው ተደረገላት። እንደ\nእኩዮቿ ሮጣ መጫወት በክፍል ውስጥ ቁጭ ብላ መማር ያቃታት ቤተልሄም እንደገና የመኖር እድልን አገኘች። በዚህም ለአራት ዓመት ያቋረጠችውን ትምህርቷን እንደገና ጀመረች፤ ዛሬ ላይ እንደ ልቧ የፈለገችውን ታደርጋለች፣ ፎቅ ላይ ትወጣለች፣ ትወርዳለች፣ ትሮጣለች፣ ትጫወታለች የስምንተኛ ክፍል ትምህርቷንም በጥሩ ሁኔታ ትማራለች። ቤተልሄም « እኔ\nቀዶ ህክምና ሳይደረግልኝ በፊት መሮጥ አይደለም መንቀሳቀስ አልችልም ነበር፤ ከታክሲ ወርጄ ወደ ሆስፒታል የምገባው እንኳን ታዝዬ ነበር፤ ዛሬ እኔ እድል ቀንቶኝ ድኛለሁ። መሰል የልብ ችግር ላለባቸው ህጻናት ግን ሊደረስላቸው ይገባል ፤ ኢትዮጵያውያን የመረዳዳት ባህላቸው ሊገለጽ ያስፈልጋል። የህክምና ባለሙያዎቹ ብቻ\nምንም ሊያደርጉልን ስለማይችሉ ሁሉም ዜጋ ሆስፒታሉን ያግዘው» ትላለች።የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ከሰኔ 1 ቀን 2011 ዓም ጀምሮ 30ኛ ዓመት\nየምስረታ በዓሉን «ስለ ልብ ብላችሁ፤ ከልብ አድምጡን!» በሚል መሪ ሀሳብ ያከብራል። ይህንን አስመልክቶም በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ሄለን በፍቃዱ እንዳሉት ሆስፒታሉ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ህጻናት ተስፋ የሆነ ቢሆንም ያለበት የአላቂ እቃዎች እጥረት በሚፈለገው ልክ እንዳይሰራ አድርጎታል። እነዚህ አላቂ እቃዎች በባህሪያቸው ለልብ ህክምና በጣም አስፈላጊ፣ በቀላሉ የማይገኙ፤ በተለይም ደግሞ አገር ውስጥ የሌሉና በውጭ ምንዛሪ የሚመጡ መሆናቸው ችግሩን እንዳባባሰው ይናገራሉ።ይህንን እቃ ለመግዛት ብዙ ብር ይጠይቃል፡፡ በመሆኑም ሁሉም ኢትዮጵያዊ « እኔ ምን ማድረግ እችላለሁ» ብሎ ማሰብ አለበት ያሉት ዶክተር ሄለን እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ አንዳንድ ብር አዋጥቶ ማዕከሉን እንደገነባው ሁሉ ዛሬም በዚህ መልኩ ገንዘብ መሰብሰብ ቢቻል ለውጥ ማምጣት ይቻላል ይላሉ፡፡በመሆኑም ማንም ሰው ግዴታ መድሀኒት መግዛት፣ መሳሪያ ማስመጣት አይኖርበትም ግን የሚችለውን በአቅሙ ድጋፍ በማድረግ ማዕከሉ በሚፈለገው ልክ ሰርቶ በወረፋ ምክንያት ከሞት ጋር ተፋጠው ያሉትን ህጻናትን ተስፋ መመለስ ይቻል ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በሌላ በኩልም በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በመደራጀት እነዚህ ለስራው እጅግ አስፈላጊ የሆኑ አላቂ እቃዎችን ከሚኖሩባቸው አገሮች ሆስፒታሎች እየሰበሰቡ በየስደስት ወሩ አልያም በዓመት እገዛ ቢያደርጉላቸው መልካም መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ሥራ አስኪያጅ አቶ ህሩይ አሊ በበኩላቸው፤ በ 1981 ዓ.ም በቅን ልቦና ተነሳስተው ምንም ደሀ ብንሆንም በልብ በሽታ መሞት የለብንም፤ በተለይም ህጻናት ተስፋቸው እንዳይጨልም በሚል ሀሳብ የተነሳሱ ሀኪሞች ከአገር ውስጥና ውጪ ባሰባሰቡት እርዳታ ማዕከሉን እውን ማድረግ ተችሏል ። የዛሬ\n30 ዓመት ስራውን በይፋ ሲጀምርም በርካታ ህጻናትን ወደ ውጭ አገር በመላክ ያሳክም ነበር፤ በዚህ ስራም ከ 2 ሺ\n300 ህጻናት በላይ የእድሉ ተጠቃሚ ሆነዋል ይላሉ።በወቅቱ ማዕከሉ አቅሙ ውስን የነበረ በመሆኑ ህጻናቱ ለህክምና ወደ ውጭ በሚሄዱበት ጊዜ አንድ የቤተሰብ አባል እንኳን አብሮ ለመላክ አይቻልም ነበር ያሉት አቶ ህሩይ፤ ይህ ደግሞ ህጻናቱ ቀዶ ህክምናቸውን ጨርሰው ከሰመመን በሚነቁበት ጊዜ የሚያዩት በመልክም በቋንቋም የማይመስሏቸውን የሌላ አገር ዜጎች ስለነበር በስነ ልቦና እጅግ ይጎዱ አንደነበር ያስታውሳሉ። የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ከ 10 ዓመት\nበፊት በህብረተሰቡ ድጋፍ እውን መሆን ከቻለ በኋላ ግን ቢያንስ ህጻናቱ በአገራቸው ላይ ከቤተሰቦቻቸው እቅፍ ሳይወጡ የህክምና አገልግሎቱን እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን የሚናገሩት ሥራ አስኪያጁ፤ ይህም ቢሆን ግን አሁንም ባለበት የአላቂ እቃዎች እጥረት ምክንያት መረዳት የሚገባቸው ህጻናት ረጅም ቀጠሮን ወስደው ወረፋ እንዲጠብቁ ተገደዋል ብለዋል። ‹‹ችግሩ ቢኖርም ቅድመ እና ድህረ ቀዶ ህክምና ላይ ያሉ ታካሚዎች ሁልጊዜ ክትትል ይደረግላቸዋል፤ ከሰኞ እስከ ረቡዕም ቀዶ ህክምና ይሰራል፡፡ በዚህም የብዙ ህጻናት የነገ ተስፋ እያለመለመ ይገኛል። በዚህ መልክ ስራውን ይስራ እንጂ ከፍተኛ በሆነ የገንዘብ እጥረት አለ ፡፡ በተለይም ደግሞ በአላቂ እቃዎች ችግር ውስጥ ነው፡፡ ማዕከሉ በገንዘብ ሲተመን ቀላል የማይባል አገልግሎትን እየሰጠ ያለ ቢሆንም እንደ አገልግሎቱ አስፈላጊነትና እንደ ህመሙ ስፋት የሚያድግበት መንገድ መፈለግ አለበት›› ይላሉ አቶ ህሩይ፡፡በክብረ በዓሉ\nላይም እስከ አሁን\nሲደረግ ለነበረው ድጋፍ\nእውቅና ለመስጠት ፤ ባለፉት\n30 ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶችን\nያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ማሳወቅና\nማዕከሉ ያለበትን የፋይናንስ\nበተለይም የአላቂ እቃዎች\nችግር ከሚመለከታቸው አካላት\nእንዲሁም ከኢትዮጵያ ህዝብ\nጋር በመሆን ለአንዴና\nለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት\nያለመ መሆኑ ተገልጿል።አዲስ ዘመን ግንቦት 23/2011", "passage_id": "ca26b62d5b712918fed284b4d7e90cd0" }, { "passage": "እናት እና ታላቅ ወንድማቸውን በጥቂት ቀናት ፍርርቅ ያጡ ህጻናትን ለመርዳት ከሰሞኑ የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች አንድ የሰብአዊነት ዘመቻ አድርገዋል። በዘመቻውም ወደ 2 ሚሊየን ብር የሚጠጋ የገንዘብ እና የዓይነት ድጋፍ ተገኝቷል።ናኮር መልካ የዘመቻውን አስተባባሪ እና ድጋፍ የተደረገለት ቤተሰብ አባላትን አነጋግሯል። ሙሉ መሰናዶውን ያዳምጡ። \n", "passage_id": "094220cd036337fbf22aa5130ecbe78e" }, { "passage": " የሞባይል ስልክ ቴክኖሎጂ በየጊዜው ይቀያየራል። ቴክኖሎጂው በአሁኑ ወቅት ብዙ አገልግሎት የሚሰጥበት ሆኗል። ገብስ ገብሱን ብጠቅስ አንኳ በሬዲዮና ቴለቪዥን የሚገኙ መረጃዎችን በስልኩ ማግኘት ይቻላል። ሰአት፣ የሂሳብ መሳሪያ እና የመሳሰሉት አገለግሎቶችም በሞባይል ስልክ ውስጥ ተቀምጠዋል። የባንክ ሂሳብ ይንቀሳቀስባቸዋል፤ የጤና ክትትል ይደረግባቸዋል፤ እረ ስንቱ። ዋጋቸው እየናረ ሆኖ እንጂ አገልግሎታቸውማ የትየለሌ ነው፤ ምን ገንዘብ ባይፈጅ ነው የተባለው። ስልኮቹ\nተፈላጊነቸው እየጨመረ በመምጣቱም በሌቦች ቀልብ ውስጥ በእጅጉ ወድቀዋል። የሞባይል ስልክ ንጥቂያ እና ስርቆት በእጅጉ ደርቷል። ዱሮ ወርቅ ከጠፋ አይገኝም ይባል ነበር፤ ዘንድሮ ደግሞ እንዲሁም ሞባይል ስልክ ቢባል በእጅጉ ያስኬዳል። የሞባይል ስልክ ጠፍቶበት የተገኘለት ጥቂት ነው ሊሆን የሚችለው። የሞባይል\nስልኮችን ደህንነት እና የደንበኞችን ሚስጢር ለመጠበቅ ሲባ ልም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ስራ ላይ እንዲውሉ እየተደረገ ነው። ባለቤቱ ብቻ እንዲከፍታቸው በሚል የማለፊያ ቃል ይዘጋጅላቸዋል፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በአሻራ የሚከፈቱበት ስርዓት ተፈጥሯል። በፊት ምስል ላይ ተመስርተው የሚከፈቱም ስራ ላይ ውለዋል። በዚያው\nልክም ይህን ሁሉ ቴክኖሎጂ ማርከሻ ይዘው የሚመጡ ሌቦችም በር ክተዋል። ሰሞኑን በቻይና አንድ ሆቴል መኝታ ክፍል ውስጥ የታየውም ይሄው ነው። አገር አማን ብሎ ስልኩን ይዞ ጋደም ያለን ሰው ጉድ ለማድረግ ሌቦች የተጠቀሙበት ዜዴም ይህንኑ ያመለክታል። በዚህ የቴክኖሎጂ ዘመን በሞባይል ስልኮች የሚፈጸም ወንጀልም\nእንዲሁ ተበራክቷል ያለው ሰሞኑን ለንባብ የበቃ የኤንዲቲ\nዘገባ ግለሰቡ አገር አማን ብሎ በተኛበት ሆቴል መኝታ ክፍል ውስጥ ሌቦች ይገባሉ። ከዚያም ስልኩ በፊት ምስል የሚከፈት\nመሆኑን ከተረዱ በሁዋላ የተኛውን ሰው ፊት በመጠቀም\nስልኩን ይከፍታሉ። ከዚያም አስር ሺ ዩዋን ከግለሰቡ\nየዊቻት የሒሳብ ቁጥር ወደራሳቸው የባንክ ሂሳብ ያዞሩና ምንም እንዳልተፈጠረ\nአርገው ወደ ስራቸው ይመለሳሉ። ወንጀሉ የተፈጸመው በቻይና ኒንግቦ ከተማ ሲሆን፣ ግለሰቡ ገንዘቡ መወሰዱን ያወቀው በማግስቱ ነበር።ወዲያውኑም ለፖሊስ ያመ ለክታል። ፖሊስ ወንጀል ፈጻሚዎቹ ላይ ለመድረስ ብዙም አልተቸገረም። ግለሰቡ ያረፈበት ሆቴል ሰራተኞች የሆኑት ሊዩ እና ያንግ በጉዳዩ ተጠርጣሪ ሆነው ይገኛሉ። ያልተለመደ የዘረፋ ድርጊት በመፈጸም ወንጀል ተጠርጥረውም በፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቻይናን ሲና የዜና አገልግልት ዋቢ ያደረገው የኤንዲቲ ዘገባ ያመለክታል። በየማለፊያ ቃሉ ያሰርናቸው የሞባይል ቀፎዎች ሲሰረቁ የሚታደገን ቴክኖሎጂና ፖሊስ እኛስ የምናገኘው መቼ ይሆን።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 8/2011", "passage_id": "4cdb187ea47d1c2f7ecc3b392ac59085" }, { "passage": "አቶ አንድአርጋቸው የ75 አመት እድሜ ባለፀጋ ነበሩ። እኝህ አዛውንት ደስተኛ ሆነው የሚኖሩና በጣም የሚያስቀና ቤተሰብ ያላቸው ሰው ነበሩ። ከብዙ አመታት በኋላ ልጆቻቸው አድገው የራሳቸውን ኑሮ በመመስረት ወደ ተለያየ አካባቢ ሄዱ። ባለቤታቸው እና የልጆቹ እናት ከብዙ አመታት በፊት በሞት ስለተለየቻቸው በመንደሩ ውስጥ በብቸኝነት እና በሀዘን ብዙ ጊዜያቸውን ያሳልፉ ጀመር። አቶ አንዳርጋቸው አብዛኛውን ጊዜያቸውን በብቸኝነት ቢያሳልፉም፤ የልጅ ልጆቻቸው በአመት በአል እና በእረፍት ጊዜያቸው አያታቸውን ሊጠይቁ ይመጡ ነበር። በዚህ ወቅት እጅግ ደስተኛ እና ተጫዋች ይሆኑ ነበር። በአንደኛው እለት አቶ አንዳርጋቸው ቀጣዩን ቀናቶች ደስተኛ ሆኖ የሚያሳልፉበት ጊዜ ተፈጠረ። ምክንያቱም አራቱ የልጅ ልጆች ሊጠይቋቸው የሚመጡበት ወቅት በመሆኑ ነበር። የልጆቹን መምጣት በጉጉት ሲጠብቁ የነበረው አዛውንት ቤቱን ማፅዳት፣ እቃዎቹን በአዲስ መልክ ማስተካከል፣ የአትክልት ስፍራዎቹን ማሰማመር ጀመሩ። ምክንያቱም እነሱን ሊጠይቋቸው የሚመጡት ልጆች ደስተኛ እንዲሆኑ ስለሚፈልጉ ነበር። የልጅ ልጆቹ የሚወዱትን የምግብ አይነትም አዘጋጅተው ይጠብቋቸው ነበር። በዚህ ጊዜ ሚስቱ ከመሞቷ በፊት የሰጠችውን «የእጅ ሰአት» ባጋጣሚ ጣሉ። ሆኖም ግን ሰአቱን ከእጃቸው ላይ መጥፋቱን ማስተዋል አልቻሉም። ሚስታቸው ከሞተች በኋላ ሰአቱን በጣም ነበር የሚወዱት ከእጃቸው ላይም እንዳይጠፋ በጣም ይጠነቀቁ ነበር። በልጅ ልጆቻቸው መምጣት በጣም ደስተኛ የሆኑት የእድሜ ባለፀጋ የሰአቱን ከእጃቸው ላይ መጥፋት ሳያስተውሉ ለቀጣዮቹ ሁለት ቀናት በደስታ እና በጨዋታ አሳለፉ። በሶስተኛው ቀን ግን ሰውነታቸውን ለማፅዳት መታጠቢያ ቤት ሲገቡ ከእጃቸው ላይ እንደሌለ ተገነዘቡ። በጣም በማዘንም እንደ አይናቸው ብሌን የሚሰስቱትን ሰአት በመጣላቸው ተበሳጩ። ለመጨረሻ ጊዜም የት ቦታ አድርገውት እንደነበር ለማስታወስ ሞከሩ። ቤቱን ለማፅዳት ሲሞክሩ ሊጠፋ እንደሚችልም ገመቱ። በግቢው ውስጥ የሚገኝ የእቃ ማከማቻ ቤት ውስጥ ሊሆን እንደሚችልም ጠርጥረው እዛው ለመፈለግ ወሰኑ። በአያታቸው ግራ መጋባት እና መናደድ የተገረሙት ልጆች፤ ምን እንዳጋጠማቸው ጠየቋቸው። እሳቸውም « ከአያታችሁ የተሰጠኝን እና በህይወቴ ትልቅ ግምት የምሰጠውን ሰአቴን ጣልኩት፤ ልክ ልቤን እንደጣልኩት ነው የሚሰማኝ። ይመስለኛል እቃ ማከማቻ ቤት ውስጥ የጣልኩ ይመስለኛል » በማለት ነገራቸው። ልጆቹም በሁኔታው ማዘናቸውን በመግለፅ፤ በፍለጋው እንደሚተባበሩ ገለፁላቸው። ልጆቹ እና አያታቸው አላስፈላጊ እቃ በብዛት የሚከማችበት ቤት ውስጥ ሊገኝ እንደሚችል ወስነው ፍለጋቸውን ቀጠሉ። ሰአቱን ለማግኘት ሁሉንም እቃ ለማየት ሙከራ አደረጉ። ሆኖም ግን የጠፋውን የእጅ ሰአት ሊያገኙት አልቻሉም። ያረጁ መፅሀፍት፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ እንዲሁም በርካታ ቁሳቁሶች በቤት ውስጥ ተከማችቶ ስለነበር ፍለጋቸውን አስቸጋሪ አድርጎባቸው ነበር። ለ ሁለት ሰአታት ያክል ሲፈልጉ ቆይተዋል። በሁኔታው እጅግ ያዘኑት አቶ አንዳርጋቸው የልጅ ልጆች ፍለጋቸውን ማቆም እንደሚኖርባቸው አስረዷቸው። ውዱን ሰአት ከእንግዲህ ሊያገኙ እንደማይችሉ ተገንዝበው ነበር። ልጆቹም በሁኔታው በጣም አዘኑ። ሆኖም ግን አያታቸው በተፈጠረው ሁኔታ እንዳያዝኑ በተቻላቸው መጠን ሊያፅናኑን ሞከሩ። ከልጅ ልጆቹ አንደኛዋ የሆነችው እና ፅጌ የምትባለዋ አስተዋይ ልጅ፤ አስቀድመው ሁሉም የእጅ ሰአቱን ሲፈልጉ የነበረበት ቤት ተመልሳ ትሄዳለች። በሁኔታው የተገረሙት አያቷ እና ወንድሞቿ ይህንን ለምን እንደምታደርግ ይጠይቋታል። ምክንያቱም እስኪሰለቻቸው ድረስ ሰአቱን ለማግኘት ሙከራ አድርገው አልተሳካላቸውም ነበር። ፅጌም ወንድሞቿ እና አያቷ ወደ እቃ ማከማቻው ቤት ሲሄዱ እንዳይከተሏት ነግራቸዋለች። ምንም አይነት ድምፅም እንዳያሰሙ ታስጠነቅቃቸዋለች። በሁኔታው የተገረሙት ወንድሞቿ እና አያቷም ፍላጎቷን ለማሳካት ይስማማሉ። ፅጌ በዝግታ ወደ እቃ ቤቱ አመራች። በሩን ከፍታም ወደ ቤቱ አንደኛው ጥግ በማምራት ያገኘችው መቀመጫ ላይ ለ25 ደቂቃዎች በቤቱ ውስጥ ከተቀመጠች በኋላ አያቷ እና ወንድሞቿ ወደሚገኙበት አካባቢ አመራች። ሁሉም ግን ከፊት ለፊታቸው በሚያዩት ነገር ተገርመው ነበር። ምክንያቱም ፅጌ ለሁለት ሰአት ያክል ለፍተው ሲፈልጉት የነበረውን የአያታቸውን ሰአት ማግኘት ችላ ነበር።አቶ አንዳርጋቸው በፍቅር የሚወዷት ባለቤታቸው የሰጠቻቸው ሰአት በመገኘቱ እጅግ በጣም ደስተኛ ነበሩ። አገኘዋለሁ ብሎም አልገመተም። ከምንም ነገር በላይ የባለቤታቸው ስጦታ እስከ ህይወታቸው ፍፃሜ እንዲቆይ ፍላጎታቸው ነበር። በሁኔታው በጣም የተደሰቱት አያቷም፤ ፅጌን ሰአቱን እንዴት እና የት ቦታ ላይ እንዳገኘችው ጠየቋት። ፅጌ ለአያቷ እንዲህ ስትል መለሰች «አያቴ በበጋ ወራት ትምህርት ቤት በጣም የምንወደው አስተማሪያችን ሁል ጊዜ ዝም የማለት ጥቅሞችን ይነግረናል። ሁሌ ባይሆንም አንዳንድ ወቅት ዝምታ አስፈላጊ መሆኑን ያስረዳናል። ለምሳሌ እሱ ሲያስተምር በጥሞና እንድናዳምጠው ይመክረናል» በማለት መለሰችለት። አያቷም ግራ በመጋባት መንፈስ « ታዲያ ይሄ ከእጅ ሰአቱ መገኘት ጋር ምን አገናኘው?» ሲሉ ጠየቋት። ፅጌ ለአያቷ ጥያቄ በድጋሚ ምላሽ ሰጠች «አያቴ የእጅ ሰአቱን ስንፈልግ እየተጯጯህን እና እቃዎችን ከወዲያ ወዲህ እያንኳኳን ነበር። ትንሽ በመሆኑም የት ቦታ ተደብቆ እንደነበር ለማወቅ አልቻልንም። ሆኖም ግን እኔ ለሁለተኛ ጊዜ ስሄድ ብቻዬን ነበርኩ። እቃዎቹን በማንኳኳትም ልፈልገው አልሞከርኩም። ቁጭ ነበር ያልኩት። ምክንያቱም የእጅ ሰአቱ ሲቆጥር «ቲክ… ቲክ… ቲክ…» የሚል ድምፅ ያሰማ ነበር። ዝም በማለቴም ይህንን ድምፅ መስማት ችያለሁ» በማለት በፈገግታ በመሞላት አስረዳቻቸው። አያቷም በሁኔታው በመደነቅ አቅፈው ግንባሯን በመሳም አመሰገኗት። በዝምታና በጥሞና ነገሮችን መከታተል፤ ረጋ ብሎ ሁሉንም ነገር ማየትና መመርመር ትክክለኛ ውሳኔ ላይ ለመድረስ እንደሚያስችልም ለሁሉም አስተማረች። አሁን በሀገራችን ያለው ሁኔታም ይሄንን የሚጠይቅ ነው። አዲስ ዘመን የካቲት 15/ 2012  ዳግም ከበደ", "passage_id": "9140e7e676cf0bc5533f32535b36f7d7" } ]
ba89894053fb4c407b57be06e93ab0a4
9cdb90956f388f1367e4ff8f0a428b05
ከ32 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጤና መድህን ሽፋን ተጠቃሚ መሆናቸው ተነገረ
ከ32 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጤና መድህን ሽፋን ተጠቃሚ መሆናቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደስ ገለጹ። በአማራ ክልል የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከልና የጤና መድህን ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የንቅናቄ ዘመቻ ውይይት እየተካሄደ ሲሆን፤ በውይይቱ የክልሉ ርዕሸ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር፣የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ ሃላፊዎች እንዲሁም የዞንና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።በዚህ ወቅት ዶክተር ሊያ ባደረጉት ንግግር፤ የጤና መድህን ሥርዓት በገጠርና በከተሞች መደበኛ ባልሆነው የኢኮኖሚ ዘርፍ ተሠማርተው ለሚገኙ ዜጎች ተጠቃሚነትን የሚረጋግጥ ሥርዓት መሆኑን ገልጸዋል። የሁሉን አቀፍ የጤና መድህን ሁለት ዋና ዋና ዓላማዎች እንዳለው የገለጹት ዶክተር ሊያ አንደኛው ከኪስ በሚወጣ ወጪ ለሚታከሙ ዜጎች ለድህነት እንዳይጋለጡና አስፈላጊውን የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ተናግረዋል።ሁለተኛው የጤና ስርዓት ዘላቂ የሆነ የገቢ ምንጭ እንዲኖረው በማድረግ ትልቅ ሚና የሚጫወት ፕሮግራም ለማድረግ ያለመ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ በሀገር ደረጃ በ2003 ዓ.ም በ13 ወረዳዎች ተጀመረው የጤና መድህን ሥርዓት በ2012 ዓ.ም በ770 ወረዳዎች ተተግብሮ 32 ሚሊዮን ዜጎች የጤና መድህን ሽፋን ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ብለዋል። ከአባላቱም 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን በመግለጽ፤ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች በጤና መድህኑ ወጪ ተሸፍኖላቸው የህክምና ጤና አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል። የጤና መድህኑ በሀገር አቀፍ ደረጃ አባላት በማፍራት ያለው አፈፃፀም 82 በመቶ ሲሆን በአማራ ክልል ያለው አፈፃፀም ደግሞ 92 መሆኑን ገልጸዋል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እንደ ሀገርና ክልል ስርጭቱ እና ወደ ፅኑ ህሙማን የሚገቡ የኮሮና ቫይረስ ህሙማን ቁጥር እየጨመረ የመጣ በመሆኑ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም ሚኒስትሯ አሳስበዋል:: የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መልካሙ አብቴ በበኩላቸው፤ የተቀዛቀዘውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የመከላከል ስራና የጤና መድህን ተደራሽነት ለማረጋገጥ ከጥር 1 እስከ 30 ቀን 2013 ዓ.ም የአንድ ወር የንቅናቄ ዘመቻ በአማራ ክልል እንደሚካሄድ ተናግረዋል:: የክልሉ ርዕስ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር በኩላቸው፤ ህብረተሰቡ በሠላም ማስከበር ያደረገውን የተቀናጀ ስራ የኮሮና ቫይረስን በመከላከልና የጤና መድህን ተደራሽነትን በማረጋገጥ ሊደግመው እንደሚገባ ገልጸዋል::የክልሉ መንግስት ከዚህ በፊት ሲያደርገው እንደነበረው ሁሉ አሁንም የኮሮና ቫይረስን የመከላከል እና የጤና መድህን ተደራሽነትን የማረጋገጥ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን የዘገበው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ነው::አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38384
[ { "passage": "አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ የተሻሻለ ንጽህናን ጥራት ባለው መንገድ ለዜጎች በማዳረስ ረገድ ከዘላቂ የልማት ግቦች ርቃ እየተጓዘች መሆኗ ተገለጸ፡፡ ትናንትና በተጀመረውና ለሁለት ቀናት በሚቆየው ዓመታዊ የውሃ አቅርቦት፣ ሳኒቴሽን፣ ሃይጅን እና የውሃ ሃብት አስተዳደር የዘርፈ ብዙ ባለ ድርሻ አካላት ዓመታዊ የውይይት መድረክ ላይ የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ሜዳ ላይ መጸዳዳትን በመቀነስና አጠቃላይ የንጽህና አጠባበቅ ሽፋንን በማሳደግ ረገድ አበረታች ውጤቶችን ያስመዘገብች ቢሆንም አገልግሎቱን ጥራት ባለው መንገድ ማዳረስ ላይ ከልማት ግቦች ርቃ እየተጓዘች መሆኗን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ለአካል ጉዳተኝነትና ለሞት ከሚዳርጉ ሦስት ዋና ዋና ምክንያቶች መካከል የውሃ አቅርቦትና\nየንጽህና አጠባበቅ ችግር አንደኛው ሲሆን፤ በሌላ በኩልም ሃያ ሁለት በመቶ የሚሆኑ ከአምስት ዓመት በታች ያሉ የህጻናት ሞት መንስኤ የሆነው የተቅማጥ በሽታ የንጽህና ጉድለት መገለጫ መሆኑን ዶክተር ሊያ ጠቁመዋል ፡፡ የንጽህና አጠባበቅ ሽፋኑን በማሳደግ ረገድ ብዙ ሥራዎች በመሰራታቸው አበረታች ውጤት መመዝገቡን የጠቆሙት ሚንስትር ዴኤታዋ፤ አገልግሎቱን በጥራት በማዳረስና ቀጣይነቱን በማስጠበቅ ረገድ አሁንም ብዙ የሚቀሩ ነገሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ ዶክተር ሊያ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመቅረፍና\nየዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ሚንስቴር\nመስሪያ ቤቱ በተለይም\nየዘርፉ ዋነኛ ማነቆ የሆነውን ትክክለኛና\nጥራት ያላቸው የንጽህና\nመጠበቂያ ቁሳቁሶች እጥረት ለመፍታት አቅርቦቱንና\nየገበያ ተደራሽነቱ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን በተያዘው የበጀት ዓመትም በተመረጡ\nሃምሳ የትራንስፎርሜሽን ወረዳዎች\nቢያንስ አንድ የንጽህና\nመጠበቂያ ቁሳቁስ አቅርቦትና የገበያ ማዕከል ለመገንባት በዕቅድ መያዙን ገልጸዋል፡፡የብሔራዊ አንድ ዋሽ መርሐ ግብርን በበላይነት የሚያስተባብረው የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው መርሐግብሩ በኢትዮጵያ መንግሥትና በልማት አጋሮች በውሃ አቅርቦት፣ ሳኒቴሽንና የአካባቢ ጤና አጠባበቅን ለማሻሻል ባለፉት አስር ዓመታት እየተተገበረ የሚገኝ ሲሆን፤ በመጀመሪያው ዙር ሦስት ነጥብ 91 ሚሊዮን ህዝብ በገጠርና ግማሽ ሚሊዮን የሚሆኑ በከተማ የሚኖሩ ህዝቦችን የተሻሻለ የውሃ አቅርቦት፣ ሳኒቴሽንና የአካባቢ ጤና አጠባበቅ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ ሚኒስትሩ ጥራት ያለው የአገልግሎት ሽፋንን ከማሳደግና ከማስፋፋት\nአኳያ አሁንም ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች መኖራቸውን ጠቁመው፤\nትኩረት ተሰጥቶ ካልተሰራ\nሃገሪቱ ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የሚቸግራት መሆኑን የዘንድሮው ዓመታዊ የዘርፈ ብዙ ባለ ድርሻ አካላት ፎረም በዚህ ላይ አተኩሮ እንደሚወያይ አብራርተዋልⵆ ውይይቱ የገጠሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በሚያስችል መልኩ የሚካሄድ መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሩ፤ አገልግሎቱ በዝቅተኛ ደረጃ የሚገኝባቸውንና በከፍተኛ ደረጃ በድርቅና በምግብ እጥረት የሚጠቁ አካባቢዎች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ፤ በዘርፉ ያሉ ፈታኝ ሁኔታዎችን በመለየትና የወደፊት ስትራቴጅካዊ የመፍትሔ ዕቅዶችን በመንደፍ አገሪቱ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ቅድሚያ ሰጥታ የምትሰራባቸውን ጉዳዮች የምትለይበትና አቅጣጫ የምታስቀምጥበት ይሆናል ብለዋል፡፡ የዘንድሮው ዓመታዊ የዘርፈ ብዙ ባለ ድርሻ አካላት ፎረም “ሁሉን አቀፍ የተቀናጀ፣ የተፋጠነና ጥራት ያለው የውሃ አቅርቦትና አስተዳደር ለዘላቂ ልማት ግቦች መሳካት” በሚል መሪ ቃል እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 17/2012 ይበል ካሳ", "passage_id": "79042864d6698e3b66a26a38aea72cdc" }, { "passage": "የመድን ፈንድ አስተዳደር ኤጀንሲ በዘንድሮው በጀት ዓመት ስድስት ወራት 115 ሺ 911 ተሽከርካሪዎች የሶስተኛ ወገን የመድን ዋስትና ሽፋን እንዲኖራቸው መደረጉን አስታወቀ።የኤጀንሲው ህዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ ሃላፊ አቶ ዘውዱ ወንድም ለዋልታ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 220 ሺ 300 ተሽከርካሪዎች ሽፋኑ እንዲኖራቸው ታቅዶ 115 ሺ 911ዱ በፕሮግራሙ ታቅፈዋል።የሞትና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች ካሣ እና የህክምና ወጪ የሚውል 9 ሚሊየን ብር በኢንሹራንስ ኩባንያዎች በኩል ገቢ እንዲሆን ታቅዶ 8 ሚሊየን 266 ሺ 340 ብር በስድስት ወራት ውስጥ ገቢ እንደተደረገም አብራርተዋል።የሞት አደጋ ለደረሰባቸው 10 ግለሰቦች ቤተሰቦች የሞት ጉዳትና ለ3 ሰዎች የአካል ጉዳት ካሳ 376 ሺ 605 ብር በስድስት ወራት ውስጥ መከፈሉንም አቶ ዘውዱ ተናግረዋል።የሶስተኛ ወገን መድን ሳይዙ ወይም ሳያድሱ በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ጠበቅ ያለ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሆነም ተናግረዋል።ከሁለት ሳምንት በፊት በተደረገ ቁጥጥርም የሶስተኛ ወገን መድን ሳይዙ ወይም ሳያድሱ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 315 አሽከርካሪዎች ተይዘው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንደሚገኝ መናገራቸውንም ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።", "passage_id": "f190447c1afaf6f76cd5916d83d22444" }, { "passage": "የአሜሪካ ዓለም ዓቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት የእናቶችና ህፃናትን ጤና ለመጠበቅ ባደረገው ድጋፍ ከአምስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን በላይ ህፃናት የተመጣጠነ ምግብ ማግኘታቸው ተመለከተ፡፡ዛሬ በሂልተን ሆቴል በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ እንደተገለፀው የተራድዖ ድርጅቱ በህፃናት አድን ድርጅት (ሴቭ ዘ ችልድረን) አማካኝነት ህፃናትና እናቶች በቅድመና ድህረ ወሊድ ወቅት የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ ለአምስት ዓመት በተተገበረው ፕሮጀክት አምስት ሚሊዮን 672ሺ ህፃናት የተመጣጠነ ምግብ አግኝተዋል፡፡ለፕሮጀክቱም የአሜሪካ ዓለም ዓቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት 50 ሚሊዮን ዶላር ወጭ ማድረጉ በመድረኩ ተገልፃል፡፡ በውጤቱም በአራት ክልሎች በተመጣጠነ ምግብ እጥረት የሚሰቃዩ ህፃናትን በ16 በመቶ ለመቀነስ ተችሏል ተብሏል፡፡ የተመጣጠነ ምግቡ ከፅንስ እስከ ሁለት ዓመት ዕድሜ ድረስ መሰጠቱም ነው የተመለከተው፡፡ፕሮጀክቱ በአማራ፣ኦሮሚያ፣ትግራይና የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መተግበሩን በኢትዮጵያ የህፃናት አድን ድርጅት ዳይሬክተር ሚስተር ጆን ግራም ገልፀዋል፡፡ በዚህም በ116 ወረዳዎች ላይ ህፃናትና እናቶች የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡እአአ ከ2011 እስከ 2016 የተተገበረው ፕሮጀክት የኢትዮጵያ መንግስት የነደፈውን ብሔራዊ የተመጣጠነ ምግብ መርሀ ግብር ማገዙን ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል፡፡ ይህም በአስተማማኝ፣በተቀናጀና በትክክለኛ መረጃ ላይ መሰረት አድርጎ መተግበሩን ተናግረዋል፡፡ህፃናት የተመጣጠነ ምግብ አግኝተው እንዲያድጉ የአሜሪካ ዓለም ዓቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በኢትዮጵያ የልማት ተራድዖ ድርጅቱ የተልዕኮ ዳይሬክተር ሚስ ሌስሊ ሪድ ተናግረዋል፡፡ተራድዖ ድርጅቱ በህፃናት አድን ድርጅት በኩል ባደረገው ድጋፍ የተመዘገበው ውጤትም የሚበረታታና የሚደነቅ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ድርጅቱ በቀጣይም አስፈላጊውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእናቶችና ህፃናት ጤና ዳይሬክተር ዶክተር ኤፍሬም ተክሌ በበኩላቸው የተመጣጠነ ምግብ በቤተሰብ ደረጃ እንዲኖር መንግስት ራሱን የቻለ መርህ ግብር ቀርፆ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡የህፃናት አድን ድርጅት ተግባርም መንግስት ለነደፈው ፕሮግራም ትልቅ መሳሪያ ሆኖ ማገዙን ነው ዶክተር ኤፍሬም ያስረዱት፡፡ በተለይም ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ለስቃይና ለህልፈተ ህይወት እንዳይዳረጉ መንግስት የጀመረውን ጥረት በማገዝ በኩል ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡በመድረኩ እንደተገለፀው በፕሮጀክቱ የአምስት ዓመት ቆይታ የተመጣጠነ ምግብ የሚያገኙ ህፃናት፣ ተገቢውን የህክምና ክትትል የሚያደርጉ ወላድ እናቶች ቁጥር ጨምሯል፡፡ የተለያዩ የጤና ክብካቤና የገቢ ማሳደጊያ ስልጠናዎችም ", "passage_id": "f38dd1a0bf99372d5e998460083e1ee2" }, { "passage": "– በኢትዮጵያ የእናቶችን ሞት በመቀነስ ረገድ ለተመዘገበው ውጤት የጤና ኤክስቴንሽን መርሃ-ግብርን እና ህብረተሰቡን ማዕከል ያደረገው የጤና ልማት ሰራዊት አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በምዕተ ዓመቱ በእናቶች ጤና አንፃር የተቀመጠው ግብ አፈፃፀም በተመለከተ  ከሐምሌ 07/006 ዓ.ም ጀምሮ የ3 ቀናት ጉባኤ በአዲስ አበባ የተካሄደ ነው፡፡ጉባኤውን የከፈቱት የኢፌዴሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ቁርጠኝነት፣ ፈጠራ የተሞላበት ስልትና ማህበረሰቡን በባለቤትነት ማሳተፍ በመቻሉ የእናቶች ሞትን በ69 በመቶ መቀነስ ተችሏል ብለዋል፡፡የተባበሩት መንግስታት ስነ-ህዝብ ፈንድ የኢትዮጵያ ተወካይ ፎስቲን ያኦ በበኩላቸው በዘርፉ በተለያየ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የሀገራት አፈፃፀም ለመገምገምና በተቀሩት ቀናት ግቡን ዳር ለማድረስ ጉባኤው አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ጠቁመዋል፡፡የቤተሰብ እቅድ አገልግሎትን ማስፋፋት፣ ያልተፈለገ እርግዝናን ማስቀረትና ወጣቶችን ማዕከል ያደረገ ስልት መቀየስ ግቡን ከዳር ለማድረስ እንደሚረዳ የመንግስታቱ ድርጅት የስነ ህዝብ ፈንድ ዋና መስሪያ ቤት አስታውቋል፡፡በጉባኤው እየተሳተፉ ያሉ 10 ሀገራት በአለም አቀፍ ደረጃ ከሚከሰተው የእናቶች ሞት 45 ከመቶ ያህሉ የሚመዘገብባቸው ናቸው፡፡ለሶስት ቀናት በሚካሄደው ጉባኤ ላይ የሀገራት ተሞክሮ ይቀርባል፡፡ የእናቶች ሞት ቅነሳ  ለማፋጠንም የድርጊት መርሃ ግብር እንደሚዘጋጅ ተገልጿል፡፡በምዕተ ዓመቱ የልማት ግብ አምስተኛ ላይ የተቀመጠውን የእናቶች ሞት ቅነሳ ግብ ሊጠናቀቅ 550 ቀናት ቀርተውታል፡፡ (ኢሬቴድ)", "passage_id": "9bc6bbf35341ebf870fe5f93dc3ffef4" }, { "passage": " ኢትዮጵያ የምዕተ ዓመቱን የጤና ግቦች ለማሳካት ባደረገችው ጥረት የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማህበር ዓይነተኛ ሚና እንደተጫወተ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ገለፁ፡፡ማሕበሩ ዛሬ የምስረታውን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ሲያከብር ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ በይፋዊ መክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት ማህበሩ የጤና ፖሊሲዎችን ባገናዘበ መልኩ ያበረከተው አስተዋፅዖ ከፍተኛ ነው፡፡በሥነተዋልዶ ትምህርት፣ የቤተሰብ ዕቅድ ተጠቃሚነት፣ የኤች አይ ቪ/ ኤድስ ሥርጭትን  እንዲሁም በወሊድ መቆጣጠሪያ ዘርፎች ማህበሩ ጉልህ ተግባራት ማከናወኑን ፕሬዚዳንቱ ተናረዋል፡፡ፕሬዚዳንቱ አክለው እንደገለጹት የእናቶችን ሞት ወደ 12 በመቶ በመቀነስ፣ በሕይወት የመኖር ዕድሜን ወደ 64 በመቶ ከፍ በማድረግ፣ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎት ተጠቃሚነትን 42 በመቶ እንዲሁም አማካይ የውልደት መጠንን 4 ነጥብ 1 በማድረስ ኢትዮጵያ ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ ቀድማ የምዕተ ዓመቱን የልማት ግቦች አሳክታለች፡፡ማህበሩ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር በተለይም የማህበራዊ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ እንዲሆን ለማስቻል መንግስት እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ፕሬዚዳንት ሙላቱ ገልጸዋል፡፡የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው በበኩላቸው ማሕበሩ በውጤታማ የጤና ፖሊሲ በመመራት ባከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት የእናቶችና ሕፃናት ሞት፣ የቲቢ፣ ወባና የኤች አይ ቪ/ ኤድስ ሥርጭትን ለመቀነስ ችሏል ብለዋል፡፡ማህበሩ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በፊት በሶስት ግለሰቦች መመስረቱን ያስታወሱት ወይዘሮ መዓዛ አሁን ከ18ሺ በላይ በጎ ፈቃደኛ አባላት እንዳሉት ተናግረዋል፡፡ በተለይም የመንግስትን የጤና ፖሊሲ መርሆችን በመከተል በማህበረሰብ አቀፍ ጤና ፕሮግራሞች ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሆነም ነው ያስገነዘቡት፡፡በመግለጫው ላይ እንደተመለከተው ማህበሩ በጤናው ዘርፍ በሰራቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት በአፍሪካ  አምስት አገሮች ከተመረጡ ተመሳሳይ ማህበራት ተርታ ለመሰለፍ በቅቷል፡፡ማህበሩ ከ90 በመቶ ያላነሰ ገቢውን ከውጭ በጎ አድራጊ ድርጅቶች እንደሚያገኝና በቀጣይ የማህበራዊ ቢዝነስ ኢንተርፕራይዞችን በማቋቋም እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ገቢ ከአገር ውስጥ ለማግኘት ማቀዱን ፕሬዝዳንቷ ጠቁመዋል፡፡ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ካሉት ክሊኒኮች፣ አገልግሎት መስጫ ማዕከሎችና በጎ ፈቃደኞች የገቢ ምንጩን ለማሳደግ ይሰራል ተብሏል፡፡ አቅም ለሌላቸው ዜጎች አገልግሎቱን በነፃ እንደሚሰጥም ነው የተመለከተው፡፡ማህበሩ ከ2008 እስከ 2012 ዓ.ም. ድረስ የሚቆይ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ አውጥቶ እየሰራ እንደሆነ ፕሬዚዳንቷ አስታውሰው በቀጣይም የማሕጸን ጫፍ በር ካንሰር ሕክምና ከተ ችግሩ እያደረሰ ያለውን ተፅዕኖ ለመቀነስ እንዲቻል ትኩረት ሰጥቶ ለመንቀሳቀስ አቅዷል፡፡በዕለቱ አውደርዕይ፣ ጥናታዊ ጽሁፎች እንዲሁም በ50 ዓመታት ውስጥ የተከናወኑ ዓበይት ተግባራትን የሚዘክር ዘጋቢ ፊልም ቀርቧል፡፡ በተጨማሪም ለማህበሩ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶች የምስጋና ሽልማትና ሰርቲፊኬት እንደተበረከተላቸው ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል፡፡ ", "passage_id": "445fa0fc34b978430c14a0aaddb392e7" } ]
db3948ec9c59c9d5a14a783e078d10bf
9c060d395d407710878ce238484a1089
ኦሊምፒክ ኮሚቴና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንደሚወያዩ ተገለጸ
በስፖርት ማህበራት ስራ አስፈጻሚዎች መካከል የሚፈጠረውን አለመግባባት ለመቅረፍ ውይይት እንደሚካሄድ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አስታወቀ። ማህበራቱ በአዋጅና በህግ የተቋቋሙ እንደመሆናቸው ህጉን አክብረው መስራት እንደሚገባቸውም ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት የውይይት መድረክ እንደሚዘጋጅም የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ጠቁሟል። የሁለቱ የስፖርት ተቋማት ስራ አስፈጻሚዎች መካከል የተፈጠረው ቅራኔ ለወራት የቆየ ሲሆን፤ በዚሁ ምክንያት ስፖርቱ በተለያዩ አመለካከቶች ለመንቀሳቀስ መገደዱ ይታወቃል። የስፖርት ቤተሰቡን በሁለት ጎራ የከፈለው ይህ ጉዳይ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ስፖርቱን አደጋ ላይ እንደሚጥለው የብዙዎች ስጋት ነበር። በቀጣዩ ዓመት እንዲካሄድ ከተራዘመው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ጋር ተያይዞ አትሌቶች ወደ ስልጠና መግባት አለባቸው በሚል ኦሊምፒክ ኮሚቴው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎችን ቢጀምርም ፌዴሬሽኑ በበኩሉ ዓለም ባለችበት የኮሮና ቫይረስ ስጋት አትሌቶችን ወደ ሆቴል ማስገባት ትክክል አለመሆኑን ገልጿል። ይህንን ተከትሎም የተቋማቱ ስራ አስፈጻሚዎች በየፊናቸው በተለያዩ ጊዜያት ተቃራኒ ሃሳቦችን በመያዝ በመገናኛ ብዙሃን መግለጫዎችን ሲሰጡ ነበር። ተቃርኖው በዚሁ ካልተገታም ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚችልም እሙን ነበር። ኦሊምፒኩ በዚህ ወቅት ይሰረዝ እንጂ፤ በየወቅቱ የሚፈጠሩትን ችግሮች ለመፍታት ኮሚሽኑ አመራሮቹን ለማነጋገር ቀጠሮ መያዙን ኮሚሽነሩ ኤልያስ ሽኩር ጠቁመዋል። ተመሳሳይ ድርሻ ባላቸው በስራ ሂደቶች ውስጥ ተቋማዊ፣ የአሰራር አሊያም በግለሰቦች መካከል አለመግባባቶች መፈጠራቸው አይቀሬ ነው። ነገር ግን ማህበራቱ በአዋጅና በህግ የተቋቋሙ እንደመሆቸው ኮሚሽኑ ያወጣውን ደንብ አክብረው መስራት አለባቸው። ስለዚህም የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት በንግግር እንዲፈታ ጥረት ይደረጋል ሲሉ ማረጋገጫቸውን ሰጥተዋል። ቀደም ሲል በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክተር የነበሩት የስፖርት ምክትል ኮሚሽነሩ ዱቤ ጂሎ በበኩላቸው፤ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አለመግባባት ከሁለት ዓመታት በላይ የቆየ መሆኑን ያስታውሳሉ። ፌዴሬሽኑም ሆነ ኮሚቴው የራሱ የስራ ድርሻ አላቸው የሚሉት አቶ ዱቤ፤ በቀጣይ ሁለቱም አካላት በየስራ ድርሻቸው እንዲሰሩ እንደሚደረግም ገልጸዋል። አዲስ ዘመን መጋቢት 19 / 2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29342
[ { "passage": "በአንድ አገር ስፖርት እድገትና ውጤታማነት ላይ ሚና ያላቸው በርካታ አካላትን መጥቀስ ቢቻልም፤ ስፖርቱን የሚመሩ አካላት መሰረት መሆናቸው ይታመናል። በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ስፖርቱ የሚመራው በሁለት አካላት ሲሆን፤ ይኸውም ህዝባዊ እና መንግስታዊ ውክልና ባላቸው ነው። ከህዝቡ የተወከሉና ስፖርቱን ለማገዝ በበጎ ፈቃዳቸው እውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ጊዜና ጉልበታቸውን የሚሰጡት አማተር ባለሙያዎች ስፖርትን በበላይነት ይመራሉ። መንግስታዊው አካል ደግሞ በስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ማህበራቱን ለመምራት በተሰጠው ስልጣን መሰረት ስራዎችን ያከናውናል። \nየመሪው አካል ጥንካሬ እና ድክመት በስፖርቱ እድገት ላይ ከፍተኛ ሚና ያለው እንደመሆኑ የስፖርት ማህበራቱ እንቅስቃሴ ወሳኝ ይሆናል። በኢትዮጵያ ስፖርት ማህበራት ባለው ሁኔታ ጥንካሬውም ሆነ ድክመቱ በአብዛኛው ከህዝባዊው አካል ጋር ማያያዝ የተለመደ ነው። ነገር ግን ከብሄራዊ እስከ ክልሎች ያሉት የስፖርት ማህበራቱ ባለሙያዎች ቅንጅት፣ ከዓለም አቀፍ ሁነት ጋር የመራመድ አቅም፣ ውድድሮችንና ስልጠናዎችን በተያዘላቸው ጊዜና ሁኔታ እንዲካሄዱ ማድረግ፣ ህግና ደንብን ባማከለ መልኩ መንቀሳቀስ እንዲሁም ለስፖርቱ እድገት መታተር ከስራዎቻቸው ጥቂቱ ናቸው። ሆኖም አብዛኛዎቹ ፌዴሬሽኖች ለውጤታማነት በአዲስ ስልትና በተሻለ ሁኔታ ከመቅረብ ይልቅ የበጀት እጥረትንና ሌሎች ጉዳዮችን እንደ እክል ሙጥኝ ማለታቸው ስፖርቱ በዘገምተኛ አካሄድ እንዲገፋ አድርጓል። \nይህንን የተመለከተው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም በዚህ ላይ እየሰራ መሆኑን ጠቁሟል። ኮሚሽኑ በቅርቡ አገር አቀፍ የስፖርት ሪፎርም ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀቱ ይታወቃል። በዚህ ላይ ተመስርቶም የስፖርት ዘርፍ የአስር ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተዘጋጅቷል። በሪፎርሙ የተጠቆሙ ጉዳዮች በእቅድ እንዲካተቱ የተደረገ ሲሆን፤ ከእነዚህ መካከል የስፖርት ማህበራትን ማጠናከር አንዱ ነው። በዚህ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ የኮሚሽኑን የቀጣይ አስር ዓመት ስራ ሪፎርሙን መነሻ በማድረግ በተለዩ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን የሚያደርግ መሆኑን ይጠቅሳሉ። ከስራዎቹ መካከል አንዱ ደግሞ የስፖርት ማህበራትን ማጠናከር ነው። \nከዚህ አንጻር በእያንዳንዱ ፌዴሬሽን የሱፐርቪዥን ዝርዝር ስራዎች የሚከናወን ይሆናል። ከዚህ በኋላም ኮሚሽኑ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የማህበራቱን ደንቦችና መመሪያዎች የማሻሻል ስራ ይሰራል። በመቀጠልም አገሪቷ ባሏትና ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን የመቀመር ስራዎችን የሚመዝን አዲስ ስታንዳርድ የሚዘጋጅ ይሆናል።\n በስታንዳርዱ መነሻነትም በብሄራዊ ደረጃ ያለ አንድ ፌዴሬሽን ምን ምን ስራዎችን እንዲያከናውን ይጠበቅበታል እንዲሁም በክልል ደረጃ ያሉ ፌዴሬሽኖች ምን ማሟላት ይገባቸዋል የሚለው በአዲስ መልክ የሚለይ ይሆናል። ኮሚሽኑም የራሱን መስፈርት የሚፈትሽ ሲሆን፤ ፌዴሬሽኖች በስታንዳርዱ መሰረት ለስፖርት ማህበርነት ብቁ ከሆኑ ይመዘገባሉ፣ ካልሆኑ ደግሞ በምዝገባው የማይካተቱ ይሆናል። \nፌዴሬሽኖቹን ተከትለው የተቋቋሙ ክለቦችም በተመሳሳይ የማጠናከር ስራም ጎን ለጎን የሚከናወን ይሆናል። ክለቦች ህዝባዊ መሰረት ያላቸው መሆኑ፣ የገቢ ምንጫቸው ከምን እንደሆነ፣ የክለብነት መስፈርቱን አሟልተው ስለመቋቋማቸው እንዲሁም ስላሉበት አጠቃላይ ሁኔታ የመፈተሽ ስራዎችም ይከናወናሉ። በታዳጊዎች የስፖርት ማሰልጠኛ ተቋማትም በተመሳሳይ ፍተሻ በማድረግ በተቀመጠላቸው መስፈርት መሰረት እንዲሰሩ የሚደረግ መሆኑንም ኮሚሽነሩ ያመላክታሉ። \nበማዘውተሪያ ስፍራዎች ልማት ላይም በተመሳሳይ ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚሰራበትና በሚማርበት አካባቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚደረግበት እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ናቸው በሚለው ላይም ምዘና የሚደረግ ይሆናል። መንግስት በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በማውጣት በሚያስገነባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ ሪፎርሙ ትኩረት ያደርጋል። በተለይ በማዘውተሪያዎች መተዳደሪያ አዋጅ ላይ የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ የሚሰራ ይሆናል። \nከዚህ ባሻገር የስራዎቹ አካል በሆኑት ሰራተኞች ላይ ክለሳ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ በተቋሙ ቢፒአር እየተሰራ ይገኛል። በስፖርቱ ልማት ላይ ለውጥ ባለመምጣቱ በሪፎርሙ ዝግጅት ወቅት በተደረገው ጥናት በተለዩ ጉዳዮች ላይ በመንተራስ ወደ ስራ ተገብቷል። መሰል ስራዎችን ማከናወን ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም የስፖርት ማህበራትን በአዲስ መልክ ማደራጀቱ ግን ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ኮሚሽነሩ አስረግጠዋል። \nምክትል ኮሚሽነሩ ዱቤ ጂሎ በበኩላቸው ከተወሰኑ ማህበራት ባሻገር አብዛኛዎቹ ያሉት በስም መሆኑን ይገልጻሉ። ዘርፉ በርካታ ችግሮች ያሉበትና ሰፊ ስራን የሚጠይቅ እንደመሆኑ ስትራቴጂካዊ አካሄድ አስፈላጊ ነው። ማህበራት ካልተጠናከሩ፣ የክለቦች አደረጃጀት ላይ ካልተሰራ፣ ታዳጊና ወጣቶችን ላይ ከላይ ጀምሮ የአሰራር ስርዓት ካልተዘረጋ እንዲሁም አካዳሚዎች ላይ የተወሰነ ስራ ሳይከናወን ውድድር ብቻ ማዘጋጀት የትም ሊያደርስ አይችልም። ስራው ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም ማህበራት ራሳቸውን የሚችሉበትን ሁኔታ ከክልል እስከ ዓለም አቀፍ ድረስ የተስተካከለ ግንኙነት ያላቸው እንዲሆኑ የሚሰራ መሆኑን ያብራራሉ።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 7/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "519cb5ef8931ca98cc474006d3a8f921" }, { "passage": " የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ከትናንት በስቲያ በተቋሙ መሰብሰቢያ አዳራሽ ከጠዋቱ አራት ሰዓት እስከ ምሽት አንድ ሰዓት የቆየ ስብሰባ አድርጓል። በ2011 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የመጣው አመራር በቆይታው ምን ምን ጉዳዮችን ሰራ፣ ምንስ ሳይሰራ ቀረ እንዲሁም ሥራዎችን በምን ደረጃ ሲከታተል ቆየ በሚል አጠቃላይ ውይይት መደረጉን ፌዴሬሽኑ ገልጿል። ከዚህ ቀደም በተቋሙ የታዩ ክፍተቶች በምን ደረጃ መስተካከል ይኖርባቸዋል፣ በሥራ አስፈጻሚው መካከል የነበረው አለመናበብ እና በቀጣይ ሊሻሻሉ የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ውይይት እንዲሁም የግል ግምገማ በማድረግ በአራት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ መተላለፉን አስታውቋል። ፌዴሬሽኑ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን የተሳታፊ ክለቦችን ቁጥር በተመለከተም ውሳኔ አስተላልፏል። ፌዴሬሽኑ\nመስከረም 05 ቀን 2012 ዓ.ም የውድድር ዓመቱ በሁለት ምድብ ተከፍሎ 24 ክለቦች እንደሚሳተፍ ያስተላለፈውን ውሳኔ በመሻር፤\nበ16 ቡድኖች መካከል ውድድሩ እንዲካሄድና በምን አግባብ መመራት እንዳለበት ከክለቦች ጋር በቅርብ ውይይት እንዲካሄድ ውሳኔ መተላለፉን\nአስታውቋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዲሲፕሊን መመሪያ ሌላው በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውሳኔ የተላለፈበት መሆኑን የገለጸው\nፌዴሬሽኑ፤ በአንድ የውድድር ዘመን ሁለት ጊዜ ፎርፌ ለተጋጣሚ ቡድኖች የሰጠ ቡድን ከውድድር እንደሚሰረዝ አስታውቋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ\nእግር ኳስ ክለብ ባለፈው የውድድር ዓመት ሁለት ጊዜ በወጣለት መርሃ ግብር መሰረት ጨዋታዎች ላይ አለመገኘቱን ፌዴሬሽኑ ከታዛቢዎች\nሪፖርት ተመልክቷል። በዚህም የሊግ ኮሚቴ ውጤቱን ለመወሰን የውድድር ክፍል በወቅቱ ባለማሳወቁ ውሳኔው ሂደት ያልጠበቀ እንዲሆን\nአድርጎታል ተብሏል። ስህተቱን በፈጠረው ሰራተኛ ላይ የዲሲፕሊን ቅጣት እንዲተላለፍበትም ተወስኗል። ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብም\nበፕሪሚየር ሊጉ እንዲቆይ እና በ2012 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እንዲወዳደር ውሳኔ ላይ መደረሱን በመግለጫው ተጠቅሷል። በአንደኛ ሊግ ተሳታፊ የነበረው ቦሌ ገርጂ እግር ኳስ ክለብ በፀጥታ ችግር ቡድኑ ወደ ጨዋታ ስፍራ\nመጓዝ ባለመቻሉ የተሰጠው ፎርፌ ቡድኑ እንዲሰረዝ ምክንያት እንደነበር ይታወሳል። ሆኖም ውድድር ክፍል ላይ በነበረው የአሰራር ክፍተት\nቡድኑ አለመጓዙ ሥራ አስፈጻሚው ስለተረዳ ቡድኑ ላይ የተሰጠው ውሳኔ እንዲሰረዝ እና በአንደኛ ሊግ እንዲወዳደር መወሰኑን ፌዴሬሽኑ\nአስታውቋል። ሥራ አስፈፃሚው\nበእለቱ ውሳኔ የሰጠበት ሌላው ጉዳይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ይመለከታል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ለኳታር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ\nወደ ሌሴቶ ሲያቀና ላጋጠመው እንግልት ምክንያት የሆኑ ሰራተኞች በጽህፈት ቤቱ በኩል በሰራተኞች አስተዳደር በዲሲፕሊን እንዲጠየቁ\nእንዲሁም በጽህፈት ቤት ኃላፊው የመጀመሪያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሰጣቸው መደረጉ ታውቋል።አዲስ ዘመን መስከረም 22/2012ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "498568db91277d14cfe37932d8f15210" }, { "passage": "የዓለም\nትልቁ ውድድር በየአራት ዓመቱ ከሚያካሂደው ኦሊምፒክ ባሻገር፤ ተጨማሪ ውድድሮችንም እንደሚያካሂድ ይታወቃል። የፓራሊምፒክ፣ የወጣቶች፣ «ስፔሻል» ኦሊምፒክ፣… ይጠቀሳሉ። በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከዛሬ ጀምሮ የሚካሄደውም በኢትዮጵያ ብዙም ዕውቅና የሌለው የስፔሻል ኦሊምፒክ ነው። ይህ ኦሊምፒክ የአዕምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ስፖርተኞች የሚያሳትፍ ሲሆን፤ ኢትዮጵያም ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳታፊ እንደምትሆን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በድረ ገጹ አስታውቋል። በዓለም ላይ ከ200 ሚሊዮን ህዝብ በላይ የአዕምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ቢኖሩም፤ በተለይ በታዳጊ ሃገሮች የተገለሉና ለከፋ ኑሮ ተጋላጭ የሆኑ ናቸው። በዚህም ምክንየት የተለያዩ ዕድሎችን እንደማያገኙ ይታወቃል፤ በዚህም በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ለማሳተፍ በሚል ኦሊምፒኩ መካሄድ ጀምሯል። እአአ በ1968 በጆን ኦፍ ኬነዲ ቤተሰቦች በአሜሪካ ሲመሰረት፤ የመጀመሪያው ውድድርም በቺካጎ ነው የተካሄደው፡፡ ላለፉት 50 ዓመታት ውድድር በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ እአአ ከ2003 ጀምሮ ከአሜሪካ ባሻገር ሌሎች ሃገራትም እየተፈራረቁ ያስተናግዱታል። ዛሬ የሚጀመረውን ውድድርም አውስትራሊያ፣ ጀርመን እና ደቡብ አፍሪካን ያሸነፈችው የዩናይትድ አረብ ኤሜሬትሷ አቡ ዳቢ ታስተናግደዋለች። በውድድሩ ላይ ከ190 ሃገራት የተወጣጡ 7 ሺ 500 አትሌቶች በ24 ስፖርቶች የሚፎካከሩ ይሆናል። ለውድድሩ\nዘጠኝ ስታዲየሞች የተዘጋጁ ሲሆን፤ የዛሬው የመክፈቻ ስነ-ስርዓትም በዛይድ ስፖርት ሲቲ ስታዲየም ይካሄዳል። የዛሬ ሳምንት የሚደረገው የመዝጊያ መርሐ ግብርም በዚሁ ስታዲየም ሲካሄድ፤ ባንዲራውም እአአ የ2021 ተረኛ አዘጋጅ ሃገር የሆነችው ስዊድን ትረከባለች። ለመጀመሪያ ጊዜ በመካከለኛዋ ምሥራቅ አገር የሚደረገው ውድድር ላይ፤ ከአትሌቶች ባሻገር 2 ሺ 500 አሰልጣኞችና የቡድን ልዑክ፣ ከ4ሺ በላይ የክብር እንግዶች ይገኛሉ። ከክብር\nእንግዶቹ መካከልም ዲዲየር ድሮግባ እና ሮማሪዮን የመሳሰሉ የእግር ኳስ ከዋክብቶች እንደሚገኙ ይጠበቃል። ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚሆን ህዝብ ደግሞ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ይከታተሉታል። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሳተፍ ሲሆን፤ በሁለት ወንድና ሁለት ሴት በድምሩ በአራት አትሌቶች ትወከላለች። በወንዶች በኩል አትሌት ብሩክ ፈለቀ እና አትሌት ሚሊዮን ያደታ፤ በሴቶች ደግሞ አትሌት ትግስት ኡጋሳ እና አትሌት መዓዛ ኤልያስ በውድድሩ እንደሚሳተፉም መረጃው ይጠቁማል። በውድድሩ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍ ሪካ 14 ሃገሮች ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሳተፉ ይሆናል። ይህ ስፖርታዊ ኩነትም ከስፖርታዊ ውድድር ባሻገር አካታች ማህበረሰብን ለመፍ ጠር የሚደረግ እንቅስቃሴም ነው።አዲስ\nዘመን መጋቢት 5/2011በብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "6ebe3c162dea369642e792a781dc9608" }, { "passage": "የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መንግሥት የአስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣ አዋጅ ቁጥር 1097/2011\nመሠረት የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የስፖርት ሥራዎችን እንዲመራ ስልጣን ተሰጥቶታል። ሚኒስቴሩ በአዋጁ የተሰጠውን ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት በማድረግ ባለፉት ሦስት ወራት እንቅስቃሴ አድርጓል። በዋነኛነት ትኩረት የተደረገው ስፖርታችን የት ላይ ነው? መንግሥታዊ አደረጃጀቱ ስፖርቱን እንዴት እየመራው ይገኛል? ስፖርቱን እንዴት ያያል? በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? የሚለውን ለመመልከት በቂ ጊዜ መውሰድ ነበረብን። በዚህ ምልከታ ውስጥ የስፖርቱ ጉዞ ቁልቁል መሆኑን መረዳት ችለናል። በዚህ ውስጥ ግን ጠንካራ ተግባራት የሉም ማለት አልነበረም። ስፖርቱን ለማንቀሳቀስ በተለየ መልኩ ሥራዎች ተሠርተዋል። ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞችን ከመገንባት፤ የስልጠና ማዕከላትን ከማቋቋምና ከማስፋፋት አኳያ ያለውን እንደማሳያ መውሰድ ያስፈልጋል። ደረጃቸውን የጠበቁ አካዳሚዎችና ማጠልጠኛ ማዕከላት፤ በፌዴራል ደረጃ የኢትዮጵያ ወጣት ስፖርት አካዳሚ እና የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ተቋቁሞ ስልጠና እንዲሰጥ ተደርጓል። በክልሎች በተመሳሳይ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል (በትግራይ ማይጨው፤ በአማራ ደብረ ብርሃን፤ በኦሮሚያ በቆጂና ሱሉልታ፤ በደቡብ ሃገረ ሰላም ወዘተ. ተገንብተዋል። በእነዚህ ተቋማት በሀገር አቀፍ ደረጃ 2 ሺህ 682 የምርጥ (ኤሊት) ስፖርተኞችና 47 ሺህ 278 ታዳጊ ወጣቶች በፕሮጀክት በመሰልጠን ላይ ይገኛሉ። በስታዲየም ግንባታ ረገድ በተመሳሳይ የሚዘረዘሩ ሥራዎች እንዳሉ ድብቅ አይደለም። ስለዚህ፤ ፖሊሲውን መሰረት በማድረግ ከተሠሩ ሥራዎች አንጻር መንግሥት የሚታማ አልነበረም። ስታዲየሞችንም ሆነ የስልጠና ማዕከላትን ማስፋፋት ብቻውን ስፖርቱን የሚያሳድግ አይሆንም። ፖሊሲውን አውቆና ተገንዝቦ ተግባራዊ የማድረግና ሌሎች መሰረታዊ ችግሮች እንዳሉበት መካድ አይቻልም። ‹የፖሊሲ አፈጻጸም ችግር አለ› የተባለውን እጋራዋለሁ። በሀገራችን የስፖርት ፖሊሲ የወጣው በ1990 ዓ.ም ነው። በየደረጃ ያሉት የጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ቢጠየቁ ፖሊሲውን በቅጡ አያውቁትም። በአብዛኛው ህብረተሰብ ዘንድም ይታወቃል ማለት አይቻልም። ፖሊሲውን ያወቀው መንግሥታዊም ሆነ ህዝባዊ አካል በፖሊሲው ውስጥ የተቀመጡትን ጉዳዮች በሚፈለገው ደረጃ ተግባራዊ አላደረገም። የስፖርት ፖሊሲው ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ 21 ዓመት አስቆጥሯል። ነገር ግን የት ደረሰ ተብሎ አልተገመገመም። አልተከለሰም። ከፖሊሲው በተጓዳኝ የሚጠቀሱ በርካታ ችግሮች ያሉ ሲሆን፤ የስፖርቱ መንግሥታዊ አደረጃጀት (ከፌዴራል ጀምሮ እስከ ወረዳ) ቁመና ጠንካራ አለመሆን፤ የስፖርቱ ህዝባዊ አደረጃጀት ስፖርትን በአግባቡ ለመምራት በሚያስችል ቁመና ላይ አለመገኘት። ይህም የስፖርት ምክር ቤቶች፣ ብሄራዊና ክልላዊ ፌዴሬሽኖች፣ ቡድኖች ወይም የህብረተሰብ ኮሚቴዎች ጠንካራ መሰረት አለመኖር፤ ከዚሁ ጋር ተያይዞ የስፖርት ህዝባዊ መሠረት አለመያዝ። ማለትም፤ በትምህርት ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች፣ በመስሪያ ቤቶች፣ በመኖሪያ አካባቢዎች፣ በአገር መከላከለያና በፖሊስ ሠራዊት… ወዘተ. ያለው አደረጃጀት ጠንካራ አለመሆን ስፖርቱን አንቀው የያዙት ችግሮች ናቸው። የስፖርት አደረጃጀቱ ቁመናው እንደ ዕድሜው አይደለም። ዘመናዊ ስፖርት ወደ ሀገራችን ከገባ ከ75 ዓመት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም፤ ዕድሜውን የሚመጥን ቁመና ላይ አይደለም። ይሄ ማለት፤ አንድ ሰው ከ70 ዓመት በላይ ከኖረ ሊኖረው የሚገባ ዕውቀት፤ ግንዛቤ፤ ነገሮችን የማመዛዘን ደረጃ ከ16 ዓመት ታዳጊ ጋር በእጅጉ ልዩነት አለው። በተቋምም ደረጃ ከተመለከትነው ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ በየደረጃው የሚገኙ ፌዴሬሽኖች እንደ ዕድሜያቸው ናቸው ወይ? አይደሉም። የኢትዮጵያን የስፖርት አደረጃጀት፤ የፌዴ ሬሽኖችን አደረጃጀት ከሌሎች ሀገራት ከኬኒያ፤ ሞሪሺየስ፤ ናይጄሪያ፤ አልጄሪያ፤ ሩዋንዳ፤ እና ከመሳሰሉት ጋር ስናወዳድር የት ነን እኛ? ካልን እታች ነን። ይህም በሀገራችን ከፍተኛ የሆነ የማስፈጸም አቅምና የትኩረት ውስንነት በመኖሩ ነው። በእርግጥ አደረጃጀት ታክቲክ ነው፤ ስትራቴጂ አይደለም። ሆኖም፤ አደረጃጀቱ የህዝብን መገኛ መሰረት በማድረግ ከታች ከወረዳ ደረጃ ትኩረት አድርጎ መሥራት ሲገባ በዚህ መልኩ አልተሠራም። ምክንያቱም ህዝብ ያለው፤ ስፖርተኛው፤ ሜዳ፤ በስፖርቱ ተሰጥኦ ያለው ሰው የሚገኘው በቀበሌ ደረጃ መሆኑ ግልጽ ነው። የስፖርቱ ዕድገት መሰረት ተብሎ በተጠቀሰው በቀበሌ ደረጃ ጠንካራ አደረጃጀት አለ ከተባለ ግን የለም። ደካማ ነው። ከፍተኛ የማስፈጸም አቅም ችግር በመኖሩ ስፖርቱ ይሄ መልክ ሊኖረው ችሏል። የተጠሪነቱን ሁኔታ ለዚህ እንደ ማሳይ መጥቀስ ተገቢ ነው። ስፖርቱ ተጠሪነቱ አንዴ ከአንዱ ይሆናል። ሌላ ጊዜ ከሌላው ይለጠፋል… ወጥ ሆኖ እንዲዘልቅ አልተደረገም። በየደረጃው ያሉ የስፖርት መዋቅሮች፤ ፌዴሬሽኖች፤ ወዘተ. የወቅቱ ቁመናቸው ዕድሜያቸውን የሚመጥን አይደለም። ከአደረጃጀት ጋር ተያይዞ ያለውን ጉድለት በሚገባ ተገንዝቦ ወደ ሥራ መግባት ያስፈልጋል። ስፖርቱን የሚመራው ህዝባዊ አደረጃጀቱ እንደሆነ በፖሊሲው ተቀምጧል። ህዝባዊ አደረጃጀት የሚባለው፤ ኦሎምፒክ ኮሚቴ፤ ፌዴሬሽኖቹ፤ ክለቦቹ፤ እንዲሁም የስፖርት ምክር ቤቶች ናቸው። በሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ የስፖርት ምክር ቤቶች የት ናቸው? ስፖርቱን በአግባቡ መምራት በሚችሉበት ቁመና አይገኙም። በፌዴራል ደረጃ የስፖርት ምክር ቤት ተቋቁሞ ወደ ሥራ የገባው በ60ዎቹ አካባቢ ቢሆንም፤ በፌዴራል ደረጃ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ ጠፍተዋል። ብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤት በ2011 ዓ.ም ነው ገና እንደአዲስ የተቋቋመው፤ በክልሎችም ተመሳሳይ ሁኔታ ይንጸባረቃል። በዓመት አንዴ፤ አሊያም ሁለቴ መሰብሰብ አለባቸው። ለአራትና አምስት ዓመታት ያልተሰበሰቡ የክልል ስፖርት ምክር ቤቶች አሉ። መገንዘብ የሚያስፈልገው በአንድ ሀገር ውስጥ ስፖርትን በበላይነት ከሚመሩ አካላት አንዱ የስፖርት ምክር ቤት ነው። ለስፖርቱ ህልውና የሆነው ይህ ምክር ቤት አለመኖሩ ትልቅ ችግር ነው። ስለዚህ ጠንካራ የስፖርት ምክር ቤት አለመፈጠር ስፖርቱ ህዝባዊ መሰረቱን እንዲያጣና አሁን ለሚገኝበት ደረጃ ምክንያት ሆኖ ይቀርባል። የስፖርት ምክር ቤት እንዲዳከም መንግሥት ፍላጎት አለው የሚል እሳቤ የለኝም። በሀገር አቀፍ ደረጃ ለስፖርት ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት ግን በእጅጉ አነስተኛ ነው። ከ83 ዓ.ም በፊት በ14 ክፍለ ሀገራት ጠንካራ የስፖርት ምክር ቤቶች ነበሩ። የየራሳቸው ዓመታዊ ውድድር ያከናውናሉ። የመላው ኢትዮጵያ ውድድሮች በስፖርት ምክር ቤት ስር ይደረጉ ነበር። ስፖርቱን በዋነኛነት የሚመራው አወዳዳሪ አካል ምክር ቤቱ ነበር። መንግሥታዊውንና ህዝባዊውን አካላት አቀናጅቶና ሚናቸውን ለይቶ አንድ ላይ እንዲጓዙ አድርጓል። በመሆኑም ስፖርቱም ህዝባዊነትን ተላብሶ በመጓዝ ውጤታማ ነበር። በአሁን ወቅት ግን፤ የመንግሥታዊና የህዝባዊ አካሉ ሚና ተደበላልቋል። በመንግሥታዊ አካሉ ስፖርቱን ከማልማት ይልቅ ስፖርቱን ለመምራት ዝንባሌ ይስተዋላል። በመገናኛ ብዙሃን የሚነገሩ ዜናዎችን ቆም ብለን ብናስብ፤ የስፖርት ውድድሮቸ ስለመደረጋቸው በተደጋጋሚ ይሰማል። ስንት ሜዳ ተስፋፋ፤ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ስንቱ ሰው ተሳትፏል፤ በትምህርት ቤት ውስጥ የሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት በአግባቡ ይሰጣል… የሚሉ ዘገባዎች ኢሚንት ናቸው። ትኩረት ያደረገው ውድድር በመምራት ላይ እንጂ በስፖርት ልማት ላይ አይደለም። መንግሥታዊ አካሉ የስፖርት ልማት የማከናወን ኃላፊነትን እንጂ፤ የመምራቱን ስልጣን ለስፖርት ምክር ቤቶች ነው የሚሰጠው፤ የመንግሥት ሚና በፖሊሲና በስትራቴጂ በማስደገፍ የህግ ማዕቀፍ በማ ውጣት በበጀትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ስፖርት ምክር ቤቶቹን፤ የኦሎምፒክ ኮሚቴን፤ ክለቦችን መደገፍ ነው። በበላይነት መሥራት የሚገባቸው ስፖርት ምክር ቤቶችና ፌዴሬሽኖች ናቸው። መንግሥታዊ አካሉ ፌዴሬሽኖችን በራሱ አምሳል ቀርጾ አስቀምጧቸዋል። በሀገ ራችን 28 ፌዴሬሽኖች ይገኛሉ። የቱ ነው ራሱን የቻለው? መንግሥታዊ አደረጃጀቱ ራሱን አላበቃም፤ አልቻለም። አብዛኛዎቹ ፌዴሬሽኖች ስትራቴጂ የላቸውም። ከክልል ጋር የሚያገናኛቸው መዋቅር በሚፈለገው ደረጃ አልተዘረጋም። ከፌዴራል ጋር ብቻ መንጠልጠሉ ውጤት አያመጣም። የታመመውን ስፖ ርት ማዳን ይቻላል። ችግሮቹ በትክክል በመኖራቸው ላይ መተማመን መቻሉ የመጀ መሪያው ደረጃ ነው። ይህ ከሆነ ህዝባዊ አደረጃጀቱም ሆነ መንግሥታዊው ወደሌሎች ጣቱን መጠቆም የለበትም፤ ወደ ራሱ መመልከት ይገባዋል። ስፖርቱ ህዝባዊ መሰረት እንዲይዝ፤ አደረጃጀቱ ጠንካራ መሰረት እንዲኖረው ማድረግ ይገባል። በፖሊሲው ላይ፤ “ህዝቡ በሚኖርበት፤ በሚሠራበት፤ በሚማርበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ማመቻቸት ይገባል፤ ይጠበቃል” ይላል። ነገር ግን፤ ህዝቡ በሚገባ ራሱ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ቢሻ ለመሥራት የሚችልበት ሜዳ የለም። ከማዘውተሪያ ስፍራ ጋር ተያይዞ ያሉትን ጉድለቶች መሙላት ያስፈልጋል። ባለሀብቱም በስፖርቱ ሊሳተፍ ይገባል። ክለቦችን በማቋቋም፤ ማዘውተሪያ ቦታዎችን በመገንባት፤ ወዘተ. መሳተፍ ከቻለ ስፖርቱን በተባበረ ክንድ ማዳን ይቻላል። በትምህርት ቤቶች ስፖርቱን ማጠንከር፤ በከፍተኛ ተቋማት ያለውን ሁኔታ ተገንዝቦ መሥራት ይገባል። የኢትዮጵያን የስፖርት ችግር በሚፈታ መልኩ እያስተማሩ እንዳልሆነ ግልጽ እውነት ነው። ስለዚህ በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠው ትምህርት በአግባቡ መሆን ይገባዋል። በሌላ ወገን፤ የስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል የስፖርት ዘርፉን እየጎዳ በመሆኑ የአገሪቱ ስፖርት የሚመራበት ወጥ የሕግ ማዕቀፍ የለም። ስለዚህ ስፖርቱን ለመምራት የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ይገባል። የስፖርት አካዳሚዎችና ማዕከላትም ስፖርቱን በሚፈለገው እንዲደግፉ ማጠናከር ይገባል። በአገራችን ስፖርት ከተጀመረ ረጅም ዕድሜ አስቆጥሯል። ስፖ ርት የአገራችንን ስም፤ ዝናና ክብር ከፍ ሲያደርግ ቆይቷል። ነገር ግን፤ ስፖርታችን በጥሩ ቁመና ላይ አይደለም። ለዘርፉ ያለው አመለካከት፤ እሳቤ ለሚጠበቅበት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ የሚመጥን አይደለም። ስፖርት ለኢኮኖሚው ያለው ፋይዳ፤ ስፖርት ማህበራዊ ትስስርን ለመፍጠር ያለውን ጠቀሜታ፤ ስፖርት ለፖለቲካው ያለውን አስተዋጽኦ በሚገባ መረዳትና አመለካከትን ማስተካከል ያስፈልጋል። የኛ ስፖርት ሰላምንና ልማትን ማገዝ ተስኖት ራሱ አጋዥ ይፈልጋል።ስፖርታችን ውስብስብ ችግሮች ያሉበት እና ጊዜ የሚፈልግ ቢሆንም ማስተካከል ይቻላል። ዋናው ጉዳይ በይቻላል መንፈስ መሥራቱ ነው። ሚዲያው ትልቅ ኃላፊነት አለበት። ስለዚህ ሁላችንም የበኩላችንን በብቃት ከተወጣን የአገራችንን ስፖርት ማስተካከል ይቻላል።ሁላችንም የየድርሻችንን በብቃት እንወጣ፤ ይህ አገራዊ ጥሪ ነው። እኔም አመሰግናለሁ!አዲስ ዘመን ሚያዝያ 2/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "6f7df1523ec430992651745bae94e00f" }, { "passage": "ዓለምን እያሳሰበ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሳቢያ መካሄድ አለመካሄዱ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አምስት ወራት የቀሩት ቢሆንም በርካታ የዓለማችን አገራት በተለያዩ ስፖርቶች የሚያደርጉትን ዝግጅት አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ኢትዮጵያም በዚህ ታላቅ የስፖርት መድረክ በተለይም በአትሌቲክስ ረጅምና መካከለኛ ርቀቶች ውጤታማ እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በቀድሞው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አባዱላ ገመዳ የሚመራ ብሔራዊ የዝግጅት ኮሚቴ በማዋቀር የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ሰንብቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውጤት በሚጠበቅበት የአትሌቲክስ ስፖርት ኢትዮጵያን እንዲወክሉ\nየተመረጡ አትሌቶች ከመጋቢት ሦስት ጀምሮ ወደ ሆቴል ገብተው ዝግጅት እንዲጀምሩ ውሳኔ ላይ መድረሱን ያሳወቀ ሲሆን፣ አትሌቶችና\nአሰልጣኞች ከትናንት ጀምሮ በኦሊምፒክ ኮሚቴ ፅሕፈት ቤት በአካል በመገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሁለት ሳምንት በፊት በኦሊምፒኩ ኢትዮጵያን የሚወክሉ\nአትሌቶችና አሰልጣኞችን መልምሎ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በመካከለኛ ርቀት፣ ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል፣ ረጅም ርቀት፣ ማራቶንና\nርምጃ ውድድሮች አሰልጣኞችና አትሌቶች መመረጣቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት\nበመካከለኛ ርቀት አሰልጣኝ ብርሃኑ መኮንን፣ ሃብታሙ ግርማ፣ ኢሳ ሽቦ እና ጉዲሳ ታሱ በአሰልጣኝነት ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም\nኃይለማሪያም እና ስንታየሁ ካሳሁን ደግሞ በተጠባባቂነት ተይዘዋል፡፡ በ3ሺ ሜትር መሰናክል ደግሞ አሰልጣኝ ተሾመ ከበደ እና ዶክተር\nብዙአየሁ ታረቀኝ ሲመረጡ አሰልጣን ከፍያለው አለሙ ተጠባባቂ ሆነዋል፡፡ አገሪቷ በኦሊምፒክ\nመድረክ በተለይ ውጤታማ በሆነችባቸው የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር ርቀቶችም አራት አሰልጣኞች ተመራጭ ሆነዋል፡፡ አሰልጣኝ ሁሴን ሸቦ፣\nቶሌራ ዲንቃ፣ ንጋቱ ወርቁ እና ኃይሌ እያሱ ሲመረጡ፤ አሰልጣኝ ተፈሪ መኮንን እና በሪሁን ተስፋይ ደግሞ የተጠባባቂነት ስፍራን\nይዘዋል፡፡ በረጅሙ የአትሌቲክስ ውድድር ማራቶን በማናጀር አሰልጣኝነት ስኬታማ የሆኑት አሰልጣኝ ሃጂ አደሎ ከሌላው ስኬታማ አሰልጣኝ\nገመዶ ደደፎ ጋር በመሆን የርቀቱን እንዲመሩም ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኝ ጌታነህ ተሰማ እና ይረፉ ብርሃኑ ደግሞ ተጠባባቂ ሆነው ተይዘዋል፡፡\nየእርምጃ ቡድኑም በሻለቃ ባየ አሰፋ አሰልጣኝነት የሚያመራ ይሆናል፡፡ ውጤት በሚጠበቅበትና\nታሪካዊ ሊሆን እንደሚችል በሚታሰበው የወንዶች ማራቶን ውድድር የ5ና 10ሺ ሜትር የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑና የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ\nአትሌት ቀነኒሳ በቀለ ባለፈው መስከረም በበርሊን ማራቶን ባስመዘገበው ፈጣን ሰዓት መሰረት በዋናነት መመረጡ የሚታወስ ሲሆን ማራቶንን\nጨምሮ በሌሎች ርቀትም ጠንካራ አትሌቶች በቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን ለመወከል ወደ ዝግጅት ይገባሉ፡፡ ከነዚህም መካከል በዶሃው\nቻምፒዮና ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው አትሌት ሞስነት ገረመው 2፡02፡55 የሆነ ሰዓት ባለፈው ለንደን ማራቶን ላይ በማስመዝገቡ በማራቶን\nቡድኑ ውስጥ በሦስተኛ ደረጃ ተመራጭ ሆኗል፡፡ ብርሃኑ ለገሰ በ2፡02፡48 በሁለተኛነት ሲመረጥ የዓለም ሻምፒዮኑ አትሌት ሌሊሳ\nዴሲሳ ከሌሎች አትሌቶች አኳያ ያለው የቅርብ ጊዜ ፈጣን ሰዓት በቡድኑ ሊያካትተው እንደማይችል ይፋ ከተደረገው የእጩዎቹ ዝርዝር\nመረዳት ተችሏል፡፡ በሴቶች ማራቶን የዱባይ ማራቶን አሸናፊዋ ወርቅነሽ ደገፋ 2፡17፡41 ሰዓት በመያዝ በቀዳሚነት ስሟ ሲቀመጥ\nሮዛ ደረጄ 2፡18፡30ና በ2፡18፡34 ሰዓት ሩቲ አጋ በቀዳሚነት ታጭተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በሚጠበቁበት\nየአስር ሺ ሜትር ውድድር የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ አሸናፊው ዮሚፍ ቀጄልቻ 26፡49፡34 በሆነ ሰዓት ሲመረጥ አንዱአምላክ\nበልሁ 26፡53፡15ና በ26፡54፡34 ጀማል ይመር በቀዳሚነት ተመርጠዋል፡፡ በሴቶች የኦሊምፒክ ቻምፒዮኗ አልማዝ አያና ከዓመት\nበላይ በጉዳት ላይ የቆየች ቢሆንም ቀዳሚዋ ተመራጭ መሆን ችላለች፡፡የዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ባለቤቷ ለተሰንበት ግደይና ነፃነት\nጉደታም ከቀዳሚዎቹ እጩዎች መካከል ተካተዋል፡፡ በወንዶች አምስት\nሺ ሜትር በዶሃው የዓለም ሻምፒዮና የወርቅና የብር ሜዳሊያ ያጠለቁት ሙክታር ኢድሪስና ሰለሞን ባረጋ እንዲሁም ሃጎስ ገብረህይወትና\nጥላሁን ሃይሌ በቀዳሚነት ሊመረጡ ችለዋል፡፡ በሴቶች ደግሞ ጸሐይ ገመቹ፣ ሐዊ ፈይሳና ፋንቱ ወርቁ ባስመዘገቡት ሰዓት መሰረት ሊመረጡ\nችለዋል፡፡ኢትዮጵያ በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ከአትሌቲክስ ውድድሮች በተጨማሪ በታሪክ\nለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ተሳታፊ መሆኗን ከሁለት ሳምንት በፊት ማረጋገጥ ችላለች፡፡ በሞሮኮ ራባት ተካሂዶ በነበረው\nየወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት የኦሊምፒክ ማጣሪያ ውድድር ማስተር ሰለሞን ቱፋ በኦሎምፒክ እንደሚወዳደር ማረጋገጡ አይዘነጋም፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 28/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "0144ad88e4be9c873dc8c3c50637e0f6" } ]
27ba3a5b65e0da6e224050b66b28fb76
a348b134447584285cd94bb502efaeaa
ብራዚላዊው ጥበበኛ በሌላ የሕይወት ምዕራፍ
  እኤአ በመጋቢት 1980 የእግር ኳስ ሀገር በሆነችው ብራዚል እግር ኳስ ወዳድ ከሆኑ ቤተሰቦች በደቡብ ብራዚል ፖርት ኤሌግሪ ተወለደ። ስሙ እንደሚያመለክተው ጠረፍ ላይ የምትገኝ አነስተኛ መንደር ነች። ይህቺ መንደር በጣም ድሃ ሕዝቦች የሚኖሩባት ናት። ቤቶቹ የተጎሳቆሉ እንዲሁም ኑሮም ከእጅ ወደ አፍ የሆነባት መንደር፡፡ በዚህች ጎስቋላ መንደር በአንድ ወቅት ወደ ዓለም እግር ኳስ ብቅ ብሎ በአጭር ጊዜ ቆይታው ዛሬም ድረስ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ልብ ውስጥ እየኖረ የሚገኘው ሮናልዲንሆ በጣም ታታሪ ቢሆንም በጣም ድሆች ከነበሩ ቤተሰቦች ተገኘ። እናቱ ዶና ሚግዌሊና ትባላለች። የቀድሞ ሥራዋ የሽያጭ ባለሙያ ስትሆን በሂደት ነርስ ለመሆን በቅታለች፡፡ አባቱ ጃኦ ለኩርዜሮ የሚጫወት ጎበዝ ኳስ ተጫዋች ነበር። ነገር ግን ዕድሜው ሲገፋና እንደድሮው ኳስ መምታት ሲያቅተው ጫማውን ሰቀለ። የድሮ ኳስ ተጫዋቾች እንዳሁኖቹ የደላቸው አልነበሩምና ደመወዛቸውም ትንሽ ስለነበር ኳስ ሲያቆሙ ኑሮን ለማሸነፍ ሌላ ሥራ መስራት ግድ ይላቸዋል። ስለዚህ ጃኦም ኳስ እንዳቆሙ ወዲያው እዚያው ወደብ ላይ የመርከብ ሠራተኛ ሆኑ። ሁለቱም በየፊናቸው እንዲህ ቢታገሉም ኑሮን ግን ማሸነፍ አልቻሉም፣ እንዲያውም እየመራቸው መጣ። ጃኦና ዶና 3 ልጆች ያላቸው ሲሆን የመጀመሪያው ልጅ ሮቤርቶ ይባላል፣ ኳስ ተጫዋችም ነበር። ሁለተኛዋ ዴሲ ትባላለች:: ሦስተኛው ልጃቸው በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችን ልናስታውሰው የወደድነው ፈገግታ ከፊቱ የማይለየው መልከ ጥፉው ነገር ግን ጥበበኛው «ትንሹ ሮናልዶ» ሮናልዲንሆ ጎቾ ነው።ሮናልዲንሆ ዕድሜው 8 ሲደርስ አባቱ ጃኦ በድንገተኛ የልብ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ሌላ ከባድ ፈተና ለድሆቹ የሮናልዲንሆ ቤተሰቦች። አሁን እቤቱን የማስተዳደር ብቸኛዋ ኃላፊነት ነርሷ እናቱ ላይ ወደቀ። ሆኖም ብዙም ሳይቆዩ በዚያው ዓመት የቤቱ ትልቅ ልጅ የሮናልዲንሆ ታላቅና ብቸኛው ወንድሙ የሆነው ሮቤርቶ ግሪሚዩ ከተባለው ክለብ ጋር ኮንትራት ተፈራረመ። በሱም ጥሩ የሚባል ገንዘብ አገኘ። ቤተሰቡም ከተጎሳቆለ ቤት ወጥተው ወደ ተሻለ ቤት ገቡ። በዚህ ጊዜ ነበር ትንሹ ሮናልዶ አዕምሮ ውስጥ አንድ ጥያቄ መመላለስ የጀመረው፡፡«ኳስ ገንዘብ የሚያስገኝ ከሆነ ለምን ኳስ ተጫዋች ሆኜ ቤተሰቤን አልረዳም?» የሚል። ጥበብ ልጇን ጠራች:: ሮናልዲንሆም ወደ ተፈጠረለት እግር ኳስ ኑሮን ለማሸነፍ በሚል ምክንያት ገባ። ትንሹ ሮናልዶ ኳስን በ8 ዓመቱ ኳስ ከሰፈሩ ልጆች ጋር በፖርት አሌግሪ የባህር ዳርቻ እንደፈለገ ያዛት ጀመር። ሜዳው ላይ በዕድሜው አነስተኛው ልጅ እሱ ነበር። ነገር ግን በችሎታው የሰውን ዓይን በቀላሉ መማረክ የሚችልና ብዙዎች ከዓይን ያውጣህ ይሉት ገቡ። እዚህም ሜዳ ላይ ነው ሮናልዲንሆ የሚለውን ስም ያገኘው። ዛሬ ላይ በመላው ዓለም መለያ መጠሪያው ይሁን እንጂ ብራዚላውያን «ሮናልዲንሆ» በሚለው ስም አያውቁትም ነበር። ትክክለኛው ሮናልዲንሆ ትልቁ ሮናልዶ ወይም «ኤልፌኖሜኖ» በሚለው ቅፅል የሚታወቀው ነው። ብራዚላውያን ስመ ረጃጅሞች ቢሆኑም አጠር አድርገው ስያሜ በመፍጠርና በማቆላመጥ ጣጣ አይወዱም። ባጭሩ መጥራት ይቀናቸዋል። የቀድሞ መሪያቸውን «ሉላ» ይሏቸዋል። ባለብዙ ጅራቱ የባህር እንሰሳ «ስኩዊድ» የሚል ትርጉም ይኑረው እንጂ ሉዊዝ ኢግናሲዮ ሉላ ዳ ሲልቫ እያሉ ጊዜ ማባከን አይፈልጉም። ሮናልዶ ሉዊዝ ናዛሪዮ ደ ሊማ ከማለት ይልቅ «ሮናልዶ» የሚቀላቸውም ለዚህ ነው። ግን ሁለት ድንቅ ሮናልዶች በአንድ ዘመን ተገኙና ብራዚላውያን ግራ ገባቸው። ያ ታላቅ ግብ አዳኝ ‹ሮናልዲንሆ› ተብሎ በሚጠራበት አገር ሌላ ‹ሮናልዲንሆ› የተባለ አስገራሚ ተጫዋች በእግር ኳስ ኮከቦች መፍለቂያ አገር ብቅ አለ። ትርጓሜው ‹ትንሹ ሮናልድ› እንደማለት ነው። ኤልፌኖሜኖ ‹ትንሹ› መባሉ አብቅቶ በዝናም፣ በክብርም ሲያድግ ብራዚላውያን ወደ ‹ሮናልዶነት› አሳደጉት።ሮናልዲንሆ እስከ 13 ዓመቱ ከሰፈሩ በዘለለ ለትልልቅ ክለቦችም ሆነ ለታዳጊ መጫወት አልቻለም። ውሎው የባህርዳርቻ ነበር። በ13 ዓመቱ ግን አንድ ነገር ተከሰተ፣ የወንድሙ ክለብ የሆነው የግሪሚዩ መልማዮች ጎበዝ ተጫዋቾችን ሊመለምሉ የነ ሮናልዲንሆ ሰፈር ደረሱ። ለምልመላው ይረዳቸው ዘንድም ተጫዋቾችን ለሁለት ከፍለው ግጥሚያ እንዲያደርጉ አዘዙ። ክፍፍሉም ፍትሃዊ እንዲሆን በሰፈር አደረጉት። የላይኛው ሰፈር ልጆችና የታችኛው ሰፈር ልጆች። ጨዋታው ተጀመረ። ልክ እንደተጀመረ ሮናልዲንሆ ተከላካዮችን አተራምሶ አስደናቂ ጎል አስቆጠረ። ከደቂቃዎች በኋላም የግል ብቃቱን ተጠቅሞ ሌላ ጎል ደገመ። ውጤቱም 23 ለ 0 ነበር። የሚገርመው 23ቱንም ጎሎች ያስቆጠረው አንድ ልጅ ነው። ሮናልዲንሆ ጎቾ ዲ አሲስ ሞሬራ!!መልማዮቹ ወደ ካምፓቸው ሲመለሱ አንድ ሳቂታ ልጅ አስከትለው ተመለሱ። ሮናልዲንሆም ከወንድሙ ጋር አንድ ክለብ ውስጥ የመጫወት ዕድል አገኘ። ሮናልዲንሆ ለታዳጊዎቹ ሮቤርቶ ደግሞ ለዋናው ቡድን፡፡ ሆኖም ብዙም ሳይቆይ ወንድሙ ሮቤርቶ በደረሰበት ጉዳት ከኳስ ተሰናበተ። ሮናልዲንሆ ወንድሙ ባጋጠመው ነገር ቢያዝንም ኳስ ከመጫወት ግን ለደቂቃም አልቦዘነም። በግሪሚዩ የእግር ኳስ ካምፕ ውስጥ ኳስን ጓደኛው አደረጋት። ቀኑን ሙሉ ውሎው ከኳስ ጋር ሆነ። ከጓደኞቹ ቀድሞ ልምምድ ቦታ መገኘት እንዲሁም ከሁሉም በኋላ መውጣት ባህሪው ሆነ።ይህ ታታሪነቱ ወደ ታላላቅ የዓለማችን ክለቦች አምርቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ በእግር ኳሱ ዓለም እስከዛሬም የማይዘነጉ ተዓምሮችን መፍጠር ቢያስችለውም ዝናና ገንዘብ ይዞት የሚመጣውን ጣጣ እንዲቋቋም አላደረገውም፡፡ ውሎና አዳሩ በየጭፈራ ቤቱ ሆነ፡፡ አብዝቶ መዝናናት ከድህነት ሕይወት ያስመለጠውን ኳስ አስረሳው፡፡ በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥም ሆኖ ግን ዓለምን በእግር ኳስ ጥበቡ ማስደመም ለእሱ ቀላል ነበር፡፡ በታላቁ ኤልክላሲኮ ታሪክም ከማራዶና በኋላ በተቃራኒ ደጋፊዎች ሜዳ የተጨበጨበለት ተጫዋች እስከመሆን ደረሰ፡፡ በኳሱ ተዝናንቶበታል፣ ተመልካቹንም አዝናንቶበታል፡፡ ይህ ሁሉ ግን ከአምስት ዓመታት በላይ እንዲዘልቅ አብዝቶ መዝናናቱ አልፈቀደለትም፡፡ ብዙዎች ጥበቡን ሳይጠግቡ የእግር ኳስ ሕይወቱ በአጭሩ ሊቀጭ ችሏል፡፡ ያም ሆኖ በትንሽ ዓመታት የሰራው ተዓምር አሁን ላይ በመጫወት ላይ የሚገኝ የትኛውም ተጫዋች ያላሳካውን ዓለም ዋንጫን፣ ባሎንዶርንና ቻምፒየንስ ሊግን ያሸነፈ ተጫዋች አድርጎታል፡፡ አሁን ላይ ግን የጎቾ ሕይወት በሌላ የታሪክ መፅሐፍ ውስጥ በአሳዛኝ ሁኔታ እየተገለፅ ይገኛል። በፓራጓይ ከተጭበረበረ የፓስፖርት ሰነድ ጋር በተያያዘ እስር ቤት ውስጥ ሆና 40ኛ ዓመቱን ባሳለፍነው ሳምንት እንዲያከብር አስገድዶታል፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29389
[ { "passage": "በልዩ የኳስ አገፋፍ ብቃቱ ይታወቃል። በእግርኳስ ሕይወቱ ለወጣት እና ለዋናው ብሄራዊ ቡድን ተጫውቷል። በክለብ ደረጃ ለጉና ንግድ፣ መድን፣ ባንኮች፣ ሐረር ቢራ፣ እና ሜታ ቢራ የተጫወተው ይህ ተጫዋች በኢትዮጵያ በተዘጋጀው የወጣቶች አፍሪካ ዋንጫ ተሳታፊ የነበረው ስብስብ አካል ነበር። ኢትዮጵያ በካሜሩን በተሸነፈችበት የመክፈቻ ጨዋታም በመጨረሻው ደቂቃ ላይ ተከላካይ እና ግብ ጠባቂ በአስደናቂ መንገድ አልፎ ባመከናት ዕድል በብዙ የእግርኳስ አፍቃሪዎች የሚታወሰው ይህ አማካይ በወቅቱ በሊጉ ከነበሩት ግብ አስቆጣሪ አማካዮች መካከል ይጠቀሳል።ሜታ ቢራ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ሲያድግ ትልቅ አስተዋፅኦ የነበረው ይህ ተጫዋች በእግር ኳስ ሕይወቱ ለአሳዳጊ ክለቡ ጉና ንግድ እና ሜታ ቢራ ልዩ ቦታ እንዳለው ይናገራል። በእግርኳስ ባሳለፋቸው ዓመታት በርካታ አይረሴ ትዝታዎች እንዳሉትና በወጣት እና ዋናው ብሔራዊ ቡድን በነበረበት ጊዜ ብዙ ትምህርት እንደወሰደም ያስታውሳል።በብዙዎች አዕምሮ ስለማትጠፋው አይረሴ አጋጣሚ ሲያወራ በቁጭት ስሜት የሚያስታውሰው ሚካኤል በሰዓቱ የነበረው ጉጉት ያለቀለትን ዕድል እንድያባክን ምክንያት እንደሆነው ገልፆ ግብ ጠባቂው እና ተከላካዩን ያለፈበት መንገድ ግን እስካሁንም ድረስ እንደማይረሳው ይናገራል። “በወጣት ብሄራዊ ቡድን በጣም ጥሩ ጊዜ ነበረኝ። በዝግጅትም፤ በውድድር ወቅትም ባሳለፍኩት ነገር ደስተኛ ነበርኩ፤ ብዙ ልምድ ወስጄበታለው። በዛ ጨዋታ ወደ ስታዲየም ከመሄዳችን በፊት በተጠባባቂ ላይ እንደምቀመጥ ሲነገረኝ ደስተኛ እና በጥሩ ስሜት ላይ አልነበርኩም። ምክንያቱም በቋሚነት መሰለፍ ይገባኝ ነበር። እንደውም ተናድጄ ወደ ስቴድየም አልሄድም ብዬ ጓደኛዬ ነው እንደምንም አሳምኖኝ የሄድኩት። ከካሜሩን ጋር የነበረው ጨዋታም ጀመረ፤ ከአሁን አሁን አሰልጣኙ ቀይሮ ያስገባኛል ብዬ ስጠብቅ ምንም ለውጥ የለም። ወደ ጨዋታው መገባደኛ ግን ምክትል አሰልጣኙ ዚያድን ጠርቼ አስገቡኝ እንጂ አልኩት ፤ ከዛ ወደ ሦስት ወይም አራት ደቂቃ ሲቀረው ቀይሮ አስገባኝ። በጉጉት ሳላሟሙቅ ሰውነቴን ሳላፍታታ ነበር የገባሁት። ከዛ ብዙም ሳልቆይ አጋጣሚው አገኘሁ… ተከላካዩቹን አለፍኳቸው… ግብ ጠባቂውም ደገምኩት… ከዛ ግን ክፍት ጎሉን ሳትኩት። 1-0 እየተመራን ነበር፤ በዛላይ በመጨረሻ ሰዓት የተገኘ አጋጣሚ ነበር። ደጋፊው አዘነ፤ እኔም በጣም አዘንኩ፤ ልቤ ተሰበረ።” ሌሎች ትላልቅ ተጫዋቾችም ግብ ጠባቂ አልፈው ጎል ይስታሉ። እንደውም በዛ ጨዋታ ከኔ በፊት ዮርዳኖስ ዓባይ ተከላካዮች አልፎ ግብ ጠባቂውንም ለመድገም አስቦ አንድ አጋጣሚ አምክኗል፤ የኔ የመጨረሻ ደቂቃ ስለሆነ ነው ብዙ የተወራለት።” ይላል አጋጣሚውን ስያስታውስ።ውድድሩ ብዙ ክስተቶች አስተናግዶ በመጨረሻም ኢትዮጵያ ወደ አርጀንቲናው ዓለም ዋንጫ በማሳለፍ ተጠናቀቀ። ሚካኤል ግን በመጨረሻው ሰዓት ወደ ዓለም ዋንጫ ከሚያመራው ስብስብ ተቀነስ፤ በጊዜው የነበረውን ሁኔታም እንዲህ ይገልፀዋል።“ከውድድሩ በኃላ አሰተያየት ተናገሩ ተብለን እኔና ሳዳት ጀማል በድፍረት የነበረውን ነገር ተናገርን። ጋርዝያቶ ጠምዶ ያዘን፤ አቶ መላኩ ጴጥሮስ የሚባሉ የወቅቱ የስፖርት ኮምሽን ኮምሽነር ደግሞ ነገሩን አጋጋሉት፤ ለምን እንዲ ብለህ ትናገራለህ ብለው ብዙ ነገር አሉኝ። ከዛ ከስብስቡ ተቀነስኩ። ደስ የሚል ጊዜ አልነበረም፤ ወቅቱን በጥሩ አላስታውሰውም። ” ይላል።ከዛ በኃላ ስለነበረው ጊዜም እንዲህ ብሏል። “ከስብስቡ ስለተቀነስኩ ጥሩ ስሜት ላይ አልነበርኩም። አንድ ቀን ቡድኑ ከአርጀንቲና ተመልሶ ከልምምድ በኃላ ጋሽ ሰውነት ቢሻው መንገድ ላይ ተገናኝተን አበረታታኝ። በሱ ብሄራዊ ቡድን ውስጥ ቦታ እንደሚኖረኝ እና በእቅዱ ውስጥ እንዳለው ነግሮኝ ተለያየን። እንዳለውም በጋሽ ሰውነት ቢሻው እየተመራን ሩዋንዳ ሄደን ሴካፋ አሸነፍን። መሬትና ሀያ ሺ ብርም ተሸለምን (በዛ ወቅት ገንዘቡ ብዙ የሚባል ነበር)። ቡድኑም በጣም አሪፍ ቡድን ነበር።በእግር ኳስ ሕይወቱ ከብዙ ኮከቦች ጋር እንደተጫወተ እና በትላልቅ አሰልጣኞች ስር እንደሰራ የሚናገረው ሚካኤል አብርሀ ስለሚያደንቃቸውም እንዲህ ብሏል። “ከተጫዋቾች አንዋር ያሲን እና ክንደያ ታመነን በጣም አደንቃቸዋለው። ክንደያ መሞቱን ስሰማ በጣም ነው ያዘንኩት። ከአሰልጣኞች ደግሞ የታዳጊ ቡድን አሰልጣኜ ሽረ እያለው ያሰለጠነኝ ግርማይ አስገዶም፣ አብርሀም ተ/ሀይማኖት እና ጋሽ ሰውነት ቢሻው በጣም አደንቃቸዋለው። በእግርኳስ ሕይወቴም ትልቅ ቦታ ነበራቸው።”ከዓመታት በፊት ወደ አሜሪካ ያመራው ሚካኤል አብርሀ በአሁኑ ወቅት በላስ ቬጋስ ኑሮውን አድርጓል።", "passage_id": "29c03e5b9cd59a454076354a3e828e17" }, { "passage": "አፍሪካ የምርጥ ደጋፊዎች እንብርት የመሆኗን ያህል የድንቅ ተጫዎቾች ባለሀብትም ነች። ከልጅነት ጀምሮ በየመንደሩ ባዶ እግራቸውን እግር ኳስ የሚጫወቱ፤ ራሳቸውን ለኳስ ፍቅር አሳልፈው የሰጡና ለእግር ኳስ ፍቅር የሚታመኑ በርካታ ተጫዋቾችን ወልዳለች። በድንቅ የእግር ኳስ ጥበብ የተካኑ በሙያቸው ብዙዎችን ያስደመሙ፣ ከአህጉሪቱም ተሻገረው በታላላቅ ሊጎች ድንቅ ችሎታቸውን ያስመሰከሩ ጥበበኞችንም አፍርታለች። እኤአ1992/93 የውድድር ዓመት በፈረንሳዩ ኃያል ክለብ ማርሴይ ከነገሠው ጋናዊው አቢዲ ፔሌ፤ አንስቶ እ ኤ አ በ1995 በዓለም አቀፉ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማት ባሎንዶር ክብርን እስከተቀዳጀው ጆርጅ ዊሃ፤አፍሪካውያን የኳስ ጠቢባን በተለያዩ የአውሮፓ መድረኮች ችሎታቸውን አሳይተዋል። በአርሰናል ቤት አይረሴ ዘመን ያሳለፈው ናይጄሪያው ኑዋንኮ ካኑ፤ በእንግሊዝ ምድር በቦልተን ወንደረረስ የነገሠው ጄጄ ኦካቻ፤በጀርመኑ ኃያል ክለብ ባየር ሙኒክ በርካቶችን ያስጨበጨበው ጋናዊው ሳሚ ኩፎር እንዲሁም በባርሴሎናና ኢንተር ሚላን ድንቅ የነበረው ካሜሮናዊው ሳሙኤል ኤቶና በቼልሲዎች መለያ ድንቅና ተአምራዊ ገድሎችን የሠራው አይቮሪኮስታዊው ዲዲየር ድሮግባ ተጠቃሾች ናቸው። የሚገባቸውን ያህል ክብርና እውቅና ማግኘት ባይችሉም በአሁኑ ወቅት የአህጉሪቱ እግር ኳስ ጥበበኞች በዓለማችን ሁሉም ማዕዘናት በተለያዩ ታላላቅ ሊጎች በመጫወት አገራቸውንና ስማቸውን ከፍ አድርገው እያስጠሩ ይገኛሉ። ብቃት ሲለካ የቆዳ ቀለም የልዩነት ተረኮች ስህተት ስለመሆናቸው በማስመስከር፤ የማንነት ሚዛንን አመጣጥነው የኃያልነት ትርጓሜ የቀየሩ፤በተለይ በፊት መስመር ተሰላፊነት ሚና የሚጫወቱ ውድ የአህጉሪቱ ኮከቦች፤ ክለቦችን ከሽንፈት መታደግና አሸናፊ ከማድረግ ባለፈ ሻምፒዮን እንዲሆኑ ማስቻላቸውን ቀጥለዋል። በተለይ ባሳለፍነው የውድድር ዓመት የአህጉሪቱ ኮከቦች ከደመቁባቸው ታላላቅ የእግር ኳስ መድረኮች መካከል ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቀዳሚ ሆኖ ይጠቀሳል። የአርሰናሉ የፊት መስመር ተጫዋች ፔር-ኤሜሪክ ኦባሚያንግ፤የሊቨርፑሎቹ ሞህ ሳላህ እና ሳዲዮ ማኔ፤በውድድሩ የካበተ ልምድ ካላቸው ከማንችስተር ሲቲው ሰርጂዎ አጉዌሮና ከቶተንሃሙ ሃሪ ኬን በላይ ከፍተኛ ግብ በማስቆጠር የሊጉ የኮከብ ግብ አግቢነት ክብርን በጋራ ተቀዳጅተዋል። በተለይ በጀርመኑ ቦርሲያ ዶርቱመንድ ቆይታው ምርጥ የፊት መስመር ተጫዋች መሆኑን በሚገባ አሳምኖ ያረጋገጠው ጋቦናዊው አጥቂ ፔር-ኤሜሪክ ኦባሚያንግ፤ በ56 ሚሊየን ፓውንድ ከሁለት ዓመት በፊት መድፈኞቹን ከተቀላቀለ ወዲህ ድንቅ ችሎታውን እያሳየ ይገኛል። ተጫዋቹ በወቅቱ የጀርመን ቆይቷውን ለመቋጨት መወሰኑ ስህተትና እንደ ቡንደስሊጋው በፕሪሚየር ሊጉ ግብ ማስቆጠር ከባድ ሊሆንበት እንደሚችል በርካቶች ቢገምቱም ተጫዋቹ ግን ይህ እሳቤ የተሳሳተ ስለመሆኑ ለማረጋጋጥ ብዙም አልተቸገረም። አርሰናል ከኤቨርተን ጋር ባደረገው ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታ የመድፈኞቹን መለያ መልበስ የቻለው ኦባሚያንግ፤ ክለቡ ጨዋታውን 5ለ1 ሲያሸንፍ በመጀመሪያ ጨዋታው የመጀመሪያ ግቡን አስቆጥሯል። በውድድር ዓመቱ አስር ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ አራት ለግብ ያለቀላቸው ኳሶችን ለቡድን አጋሮቹ ማጋራት ችሏል። ተጫዋቹ በተለይ በ2018/19 የእንግሊዝ ፐሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመት ድንቅ ግብ የማግባት ችሎታ እንዳለው ይበልጥ ያስመሰከረ ሲሆን፤ለመድፈኞቹ በ36 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 22 ግቦችን አስቆጥሯል። አምስት ለግብ ያለቀላቸው ኳሶችን ለቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል። ተጫዋቹ ያስቆጠራችው ግቦችም የሊጉን ኮከብ ግብ አግቢነት ክብር እንዲቀዳጅ አስችለውታል። በአሁኑ ወቅትም በዓለማችን ታላቁ ሊግ የአገሩንና የራሱን ስም ከፍ አድርጎ እያስጠራ ይገኛል። ሌላኛው በአሁኑ ወቅት በታላቁ ሊግ ድንቅ ችሎታቸውን በማስመሰከር ላይ የሚገኘው የአህጉሪቱ ፍሬ ጥበበኛው ሰይዲ ማኔ ነው። ከ2014/15 የውድድር ዓመት ጀምሮ በሊጉ ባለሁለት አሃዝ ግቦችን ከመረብ ማሳረፍ የማይሳነው ሴኔጋላዊው ኮከብ ማኔ፤ በተለይ በ2016 ከሳውዝሃፕተን ሊቨርፖሎችን ከተቀላቀለ ወዲህ ስሙ እጅጉን ከፍ ብሎ መሰማት ጀምሯል። በሜዳ ላይ ታታሪነቱና የተቃራኒ ቡድን ተከላካዮች በማስጨነቅ የሚታወቀው ሴኔጋላዊው ኮከብ፣ ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ከክለቡ ጋር የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ በማንሳት ማጣጣም የቻለ ሲሆን፣ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊጉ ኮከብ ግብ አግቢነት ክብርን በመቀዳጃት የወርቅ ጫማውንም ተሸልሟል።ብቃቱንና አስተዋፆኦውን በየጊዜው እያጎለበተ የሚጓዘው ሴኔጋላዊ ተጫዋች፤የብቃቱንና የአስተዋፅኦውን ያህል ባይዘመርለትም ሊጉን ከሚያደምቁት ድንቅ አፍሪካውያን ተጫዋቾች አንዱ ሆኗል። በአሁኑ ወቅት በድንቅ የእግር ኳስ ጥበብ ችሎታ ከተካኑ እና በሙያቸው ብዙዎችን ካስደነቁ አፍሪካውያን ኮከቦች መካከል በግንባር ቀደምትነት ስሙ ይነሳል። ግብፃዊው ሞሃመድ ሳላህ። የ26ዓመቱ ግብፃዊው ኮከብ በመጀመሪያ ዓመት የአንፊልድ ቆይታም በ38 ጨዋታዎች 32 ግቦችን ማስቆጠር የቻለ ሲሆን ይህም በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከሠላሳ ግቦች በላይ በማስቆጠር በታሪክ ብቸኛው ተጫዋች እንዲሆን አስችሎታል። ምትሐተኛው ግራ እግር ባሳልፈነው የውድድር ዓመት መጀመሪያ ደካማ የሚባል አቋም ማሳየቱን ተከትሎ «የአንድ ውድድር ዓመት አንበሳ» በሚል በበርካታ ወገኖች ትችት ቢሰነዘርበትም፣እያደር ብቃቱን በማረጋገጥ በብቃቱ የማይዋዝቅ ስለመሆኑ አስመስክሯል። በእግር ኳስ ጥበብ ልህቀቱ ዓለምን ያስደመመውና ሁልጊዜም ግብ ማስቆጠር የማይሳነው ሳላህ ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ክለቡ ሊቨርፑል የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ከፍ አድርጎ እንዲስም የላቀ ሚና ተጫውቷል። በግሉም ፕሪሚየር ሊጉ ኮከብ ግብ አግቢነት ክብርን በመቀዳጃት የወርቅ ጫማውን አጥልቋል። በአሁኑ ወቅት በዘመናዊ እግር ኳስ ከሚጫወቱ ከፊት መስመር ተጫዋቾች ተመራጭ መሆኑ የሚመሰከርለት ሳላህ፤ የእግር ኳስ ጥብብ ችሎታውን ያህል ዓለም ስለእርሱ የምትዘምረው በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ ስለመሆኑም ይገለጻል። ከእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውጪ በአሁኑ ወቅት በሌላ ማዕዘን በማንፀባረቅ ላይ ከሚገኙ ጥቁር ኮከቦች መካከል ስሙ ጎልቶ የሚነሳው ሌላኛው ተጫዋች ኒኮላስ ፔፔ ነው። በፈረንሳዩ ክለብ ሊል ድንቅ ተጫዋች መሆኑን እያስመሰከረ የሚገኘው አይቮሪኮስታዊው ኮከብ ፤ባሳለፍነው የውድድር ዓመት 19 ግቦችን ሲያስቆጥር፤11 ለግብ የተመቻቹ ኳስችን ለቡድን አጋሮቹ ማቀበል ችሏል። «እርሱን በተቃራኒ መለያ መግጠም እጅግ አድካሚና ፈታኝ ስለመሆኑ ብዙዎች የሚመሰክሩለት የ23 ዓመቱ ፔፔ፤ክለቡ በፈረንሳይ አንደኛ ሊግ በሁለተኝነት እንዲጨርስ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። በፈረንሳይ ሊግ አንድም «ምርጡ የአፍሪካ ተጫዋች ነህ» የሚል ክብር ተቀዳጅቷል። የተጫዋቹ ወቅታዊ ብቃትም የበርካታ ወገኖችን አድናቆት እንዲያገኝ ከማስቻሉ በተጓዳኝ የታላላቅ የአውሮፓ ክለቦችን ቀልብም እንዲሰርቅ አርጎታል። ተጫዋቹም በቀጣዩ የውድድር ዓመት ወደ እንግሊዝ በማቅናት ሊቨርፖሎችን እንደሚቀላቀል ይጠበቃል። ሞሮኮአዊው ሀኪም ዚያችም በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ምርጥ ተጫዋቾች ባለቤት ስለመሆኗ እያስመስከረ የሚገኝ ወጣት ኮከብ ነው። በሆላንዱ ክለብ አያክስ በሚያሳየው ድንቅና ውበት ያለው እግር ኳስ ችሎታው የበርካቶችን ቀልብ በቀላሉ ያገኘው ዚያች፡፡ ክለቡ የኤርዲቪዜዎን ዋንጫ እንዲያነሳ የላቀ ሚና ተጫውቷል። ባሳለፍነው የውድድር ዓመት 21 ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ 24 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ለቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ አጋርቷል።ይህም የክለቡ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋችነት ክብርንም አስግኝቶለታል። አሁኑ ላይ በርካታ ክለቦች ተጫዋቹን በዓይነ ቁራኛ በመከታተል የተጠመዱ ሲሆን፤ ተጫዋቹም ስሙ ከአርሰናል ጋር በጥብቅ እየተዛመደ ይገኛል። ሴኔጋል ዳካር ውስጥ የተወለደው የ27 ዓመቱ ተጫዋች ምቤይ ዲያን በቱርክ ሊግ ገናና ስሙን እየገነባ ነው። በውድድር ዓመቱ 29 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 30 ግቦችን ከመረብ ማሳረፍ የቻለ ሲሆን፣ ይህ የግብ የማስቆጠር ብቃቱ ሲመዘንም በእያንዳንዱ 81 ደቂቃ አንድ ግብ ማስቆጠር እንደሚችል አረጋግጦለታል። በቱርክ ሱፐር ሊግ ለጋላታ ሰራይ የሚጫወተው ኮከብ፤ ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ክለቡ ካስቆጠራቸው ግቦች መካከል 45 በመቶ የሚሆኑት ከእርሱ እግር ስር የወጡ ስለመሆናቸውም ተመላክቷል። ተጫዋቹ ለአራት ዓመት የሚያቆየው የውል ስምምነት ከኢስታንቡሉ ኃያል ክለብ ጋር ቢኖረውም፣ በርካታ አውሮፓውያን ኃያላን ክለቦችም ተጫዋቹን የግላቸው ለማድረግ አሰፍስፈዋል። በጀርመን ቡንደስሊጋ ለሆፈኒየም የሚጫወተው አልጄሪያዊው ኢሻክ ቤልፎዲልም፣ በአሁኑ ወቅት በድንቅ እግር ኳስ ችሎታቸው ዓለምን ማነጋጋር ከጀመሩ አፍሪካውያን ኮከቦች አንዱ ነው። ተጫዋቹ ባሳለፈነው የውድድር ዓመት ለክለቡ 28 ጨዋታዎች ላይ የመሰለፍ ዕድል አግኝቶ 16 ግቦችን ከመረብ አዋህዷል። አምስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ለጓደኞቹ አመቻችቶ አቀብሏል። የተለያዩ የሜዳ ላይ ኃላፊነቶችን በብቃት የሚወጣውና «የትም ቦታ ተሰልፎ ቢጫወት ግብ ማስቆጠር አይከብደውም» የሚባልለት ኮከብ፤በቡንደስሊጋው ከፍተኛ ግብ ካስቆጠሩ ሦስት ተጫዋች መካካል ስሙን አፅፏል። በቤልጂየም ሊግ ድንቅ ብቃቱን በማሳየት ላይ የሚገኘው ሌላኛው አፍሪካዊ ኮከብ ማብዋና ሳማታ ነው። ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ውስጥ የተወለደው ተጫዋቹ ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ለከለቡ 28 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 20 ግቦችን በስሙ አስመዝገቧል። የቀድሞው የአርሰናሎች ምልክት ቴሪ ዳንኤል ሄነሪ አድናቂ የሆነው ተጫዋቹ፣ በቅርቡ በቤልጂም ሊግ ከተከሰቱ አፍሪካውያን ተጫዋቾች መካከል ‹‹አንተ ምርጡ ነህ» በሚል የኮከብነት ክብር ማግኘት ችሏል። የሚገባቸውን ያህል ክብርና\nእውቅና ማግኘት ባይችሉና\nበምዕራባዊያኑ ተፅእኖ ስር\nለመደበቅ ቢገደዱም በአሁኑ\nወቅት እነዚህ የአህጉሪቱ\nእግር ኳስ ጥበበኞች\nበዓለማችን ታላላቅ ሊጎች\nአገራቸውንና ስማቸውን ከፍ\nአድርገው እያስጠሩ ይገኛሉ።አዲስ ዘመን ሰኔ\n25/2011 ", "passage_id": "3c7a29db0e8079a9638229cc8bcafacb" }, { "passage": "ከአዲስ አበባ በ110 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው ወንጂ ከተማ በእግር ኳሱ በርካታ ተጫዋቾችን ማፍራቷ ይነገርላታል። ይህም ከተማዋ ከምትታወቅበት ጣፋጭ የሸንኮራ አገዳ አምራችነቷ፣ የስኳር ፋብሪካ ማዕከልነቷ ትይዩ የእግር ኳስ ተጫዋቾች መፍለቂያ አሰኝቷታል። የወንጂን ከተማ በእግር ኳሱ ካስተዋወቁት ተጫዋቾች መካከል ደግሞ አንጋፋው ተጫዋች ተስፋዬ ኡርጌቾ ይጠቀሳል። በወንጂ ከተማ ተወልዶ ያደረገው ተስፋዬ፤ በእግር ኳሱ ትልቅ ቦታ መድረስን የልጅነት ህልሙ አድርጎ የተነሳ መሆኑን የቅርብ ወዳጆቹ ይናገሩለታል። ከልጅነቱ ጀምሮ ለእግር ኳስ ልዩ ፍቅር በመያዝ መነሻው ከሰፈር ሜዳ ነበር። በኳሱ የመጓዝ ህልሙ ሩቅ የሆነው የትናንቱ ታዳጊ ተስፋዬ፤ በስፖርቱ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በማጎልበቱ ወደ ክለብ እንዲያድግ አጋጣሚን አገኘ። \nከከተማዋ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መሠረት አንዱ የሆነው የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ያቋቋመውን «የወንጂ ስኳር እግር ኳስ ክለብ» ነበር የተቀላቀለው። ተስፋዬ የወንጂ ስኳርን መቀላቀሉ በኳሱ ለሚያልመው ህልሙ፣ ለሰነቀው ተስፋ እውን መሆን መንደርደሪያውን የትውልድ ከተማው ሆነለት። ከክለቡ ጋር የተወሰኑ ጊዜያትን ቆይታ ካደረገ በኋላ የሕይወቱ አቅጣጫ ወደ ሌላ ምዕራፍ ተሸጋገረ። በወንጂ ስኳር እግር ኳስ ክለብ በፈጣንና ጥበብ የተሞላበት እንቅስቃሴ ባለቤትነቱ በአየር ኃይል እግር ኳስ ቡድን እይታ ውስጥ አስገባው። በወቅቱ የአየር ኃይል አሰልጣኝ የነበረው አንጋፋው አሰልጣኝ ሀጎስ ደስታ ልብ በማሸነፍ አሰልጣኙ አየር ኃይልን እንዲቀላቀል አስቻለው። በእግር ኳሱ ትልቅ ደረጃ የመድረስ ተስፋ በልቡ ሰንቆ ወደሜዳ ለሚመጣው ታዳጊ ትልቅ ዕድል ነበር። \nበአየር ኃይል ቤት ተስፋዬ ምኞቱን መኖር ለመጀመሩ መንደርደሪያው ነበር። በቡድኑ ውስጥ ያሳየው እንቅስቃሴ ክለቡ እንዲደሰትበት ከማድረግ አልፎ፤ ለብሔራዊ ቡድን እንዲጫወት ሀገራዊ ጥሪ እንዲቀርብለት አድርጎታል። በ1983 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ወጣት ብሔራዊ ቡድን በመመረጥ በግብጽ አዘጋጅነት በተካሄደው 7ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ችሏል። የወንጂው ፍሬው ተስፋዬ የስኬት ጀንበርን በአጭር ጊዜ ውስጥ መመልከት የቻለ ሲሆን፤ በሜዳ ላይ የሚያሳየው ብቃትና የተላበሰው መልካም ስብዕናው ተደምረው ጉዞው ያማረ እንዲሆን አደረጉት። የወጣት ብሔራዊ ቡድኑ በሻምፒዮናው ላይ ከተሳትፎ መልስ የተስፋዬ የክለብ መዳረሻ ከአየር ኃይል ተወርውሮ ወደ አንጋፋው ቅዱስጊዮርጊስ ላይ አረፈ። በ1983 ዓ.ም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አንፀባራቂ ታሪክ ባላቸው በኢንስትራክተር መንግሥቱ ወርቁ አማካኝነት ክለቡን ተቀላቀለ። የእግር ኳሱ ጥበበኛ ተስፋዬ ፈረሰኞቹን መቀላቀሉ በኳሱ የስኬትን ቁንጮ ለመቆናጠጥ ትልቅ ዕድል ፈጥሮለታል። በአማካይና የተመላላሽ ቦታዎች ላይ በመጫወት ክለቡን ለስኬት ማብቃት በመቻሉ የክለቡ ደጋፊዎች ዛሬም ድረስ ትልቅ ቦታ እንዲኖራቸው አድርጓል። \nከ1983 ዓ.ም እስከ 1992 ዓ.ም ፈረሰኞቹን ማገልገል የቻለው አመለሸጋው ተስፋዬ፤ በቆይታው ከፍተኛ ዝናና ተወዳጅነት አትርፏል። በፈረሰኞቹ ቤት በቆየባቸው የሰባት ዓመታት ቆይታ ውስጥ በ1986 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሻምፒዮን ኮከብ ተጫዋችነትን ክብር አግኝቷል። ክለቡ ቅዱስጊዮርጊስ ከ1986 እስከ 88 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሻምፒዮናነትን ክብር ሲቀዳጅ ግብ አስቆጣሪ ከሆኑት ተጫዋቾች ጀርባ የእርሱ ሚና ግዙፍ እንደነበር በወቅቱ የነበሩ ተጫዋቾች መስክረውለታል። ከክለቡ ስኬት ተሻግሮም ለሚወዳት ሀገሩ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተመርጦ በርካታ ጨዋታዎችን ተጫውቶ አሳልፏል። \nበ1985 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ ናይጄሪያን 1ለ 0 ስታሸንፍ ብቸኛዋን ግብ በማስቆጠር ሀገሩን ለድል ያበቃበት አጋጣሚ በአብዛኛው የስፖርት ቤተሰብ ዘንድ ይታወሳል። በብሔራዊ ቡድን ብሎም በክለብ ደረጃ የነበረው እንቅስቃሴ ከክለቡ ተሻግሮ በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ ከፍተኛ ተደናቂነት ማትረፍ የቻለ ተጫዋች ነበር። በሀገር ውስጥ የክለብ ፍልሚያዎች በፈረሰኞቹ ቤት በ4 ቁጥር ማሊያ መንገስ ችሏል። በሜዳ ላይ ፈጣንና ድንቅ እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑን ተከትሎ «ተምዘግዛጊው ሚሳኤል» የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው ተስፋዬ፤ ከሀገር አልፎ ወደ አውሮፓም አምርቶ በፊንላንድ ሊግ መጫወት ችሏል። በኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ዛሬም ድረስ እንደ ብርቅ በሚታየው የአውሮፓ ሊግ የኳስ ጥበበኛው ተስፋዬ ባህር ተሻግሮ። \nእግር ኳስን በተጫወተባቸው ዓመታቶች በመሀል ሜዳ የጨዋታ ብቃቱ የብዙዎቹን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎችን ቀልብ ይስብ የነበረው፤ ተስፋዬ የተጫዋችነት ዘመኑን ቢያበቃም ከኳሱ አልተለየም ነበር። ከተጫዋችነት ወደ አሰልጣኝነት የሕይወቱ አቅጣጫ ተሸጋገረ። በአሰልጣኝነትም ሕይወት በመሰማራት የጌታ ዘሩን የታዳጊ ፕሮጀክት እና የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲንም ክለብን በመያዝ አሰልጥኗል። የሕይወቱን ፍጻሜ ከኳስና ከእናት ሀገሩ ለመነጠል ፍላጎት ያልነበረው ተስፋዬ፤ መኖር ግድ ነበርና በአሜሪካ በስደት በርካታ ዓመታትን አሳልፏል። «ተምዘግዛጊው ሚሳኤል» በገጠመው ህመም ከሚኖርበት አሜሪካ የመጣ ሲሆን፤ በሚወዳት ሀገሩ በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 05 ቀን 2012 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሕይወቱ አርፏል። በኢትዮጵያ የእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የራሱን አሻራ ማሳረፍ የቻለው ተስፋዬ የቀብር ሥርዓቱ በትውልድ ከተማው ወንጂ ሸዋ ኪዳነ ምህረት ከትናንት በስቲያ ተፈጽሟል። የተስፋዬ ሞት ብዙዎቹን ያሳዘነም ሲሆን የዝግጅት ክፍላችን በተስፋዬ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቹ ለወንድሙ ተከተል ኦርጌቾና ለመላው ስፖርት አፍቃሪ እና ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች መፅናናትን ይመኛል።\nአዲስ ዘመን ግንቦት 7/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "ecca94964ee2573c01afae2acf372265" }, { "passage": "የ32 ዓመቱ ሜሲ ባሎንዶርን ሲያሸንፍ እ.አ.አ. ከ 2015 በኋላ የመጀመሪያው ሲሆን ለክለቡና ለአገሩ 54 ግቦችን በማስቆጠር ባለፈው ዓመት ደግሞ ከባርሴሎና ጋር የላሊጋው አሸናፊ መሆን ችሏል።\n\n• ማንችስተር ዐይኑን የጣለባቸው የአቶ ምሥጢረ ኃይለሥላሴ ልጆች\n\n• ተሰናባቹ ኡናይ ኤምሪን ሊተኳቸው የሚችሉ 7 አሰልጣኞች \n\nየሊቨርፑሉ ተከላካይ ቨርጂል ቫን ዳይክ ደግሞ በዚህ ዓመት ሁለተኛውን ቦታ መያዝ ችሏል። አምስት ጊዜ ባሎንዶርን ማሸነፍ የቻለው የጁቬንቱስና የፖርቹጋር አጥቂው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ሦስተኛ መሆኑ ታውቋል።\n\nበሴቶች ደግሞ ከአሜሪካ ጋር የዓል ዋንጫን ማሸነፍ የቻለችው ሜገን ራፊኖ የባሎንዶር አሸናፊ ስትሆን እንግሊዛዊቷ ሉሲ ብሮንዝ ሁለተኛ ሆናለች። \n\nየሊቨርፑሉ ግብ ጠባቂ ብራዚላዊው አሊሴን ቤከር ምርጥ በረኛ ሲባል ጀርመናዊው የባርሴሎና ግብ ጠባቂ ማርክ ቴር ስቴገን እና ብራዚላዊው የማንቸስተር ሲቲ በረኛ ኤደርሰን ሁለተኛና ሦስተኛውን ቦታ ይዘዋል። \n\nየጁቬንቱሱ የመሀል ተከላካይ ደ ሊክት ከ21 ዓመት በታች ምርጥ ተጫዋች ተብሎ በቀድሞ ባሎንዶር አሸናፊዎች ተመርጧል።\n\nሜሲ ዘንድሮ የባሎንዶር አሸናፊ ሲሆን ውድድሩን ለ11ኛ ተከታታይ ጊዜ ከስፔን ላሊጋ የመጡ ተጫዋቾች እንዲያሸንፉ አድርጓል። \n\n• ከመጠጥ ቀጅነት ወደ እንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን \n\nሜሲ በሽልማቱ ወቅት ''ምንም እንኳን ባሎንዶርን ያሸነፍኩት ለስድስተኛ ጊዜ ቢሆንም በጣም የተለየ ደስታ ተሰምቶኛል። ባለቤቴ ሁሌም ቢሆን ትልቅ ህልም እንዲኖረን ትነግረኛለች፤ ለዚህም እራሴን በጣም ዕድለኛ አድርጌ ነው የምቆጥረው።'' \n\nሜሲ ለባርሴሎና እስካሁን 700 ጊዜ ተሰልፎ የተጫወተ ሲሆን በስሙም 614 ግቦችን አስቆጥሯል። ከቡድኑም ጋር 10 የላሊጋና አራት ቻምፒየንስ ሊግን ጨምሮ 34 ዋንጫዎችን ማንሳት ችሏል። \n\n ", "passage_id": "88250a1628ca48ae3444e1a14be8c167" }, { "passage": " አለማችን ከሊዮናርዶ ዳቪንቺ እስከ ፓብሎ ፒካሶ ድንቅ ሰአሊያንን አፍርታለች። አሁንም በየሃገራቱ በተለያዩ የስነ ስዕል ዘርፎች የስዕል ጥበባቸውን ለዓለም የሚያሳዩ ዝነኛ አርቲስቶች አልጠፉም። ሃገራችንም ብትሆን ሰዓሊና ባለቅኔ ገብረ ክርስቶስ ደስታን ጨምሮ በርካታ አንጋፋና ወጣት የስነ ስዕል ጥበበኞችን አፍርታለች። ሰዓሊያን በተለያየ የስነ ስዕል ዘርፍ የየራሳቸውን የአሳሳል ዘይቤ በመከተል የስዕል ስራቸውን የሚሰሩ ቢሆንም፣ አብዛኞቹ ቀለም ነክረው በዘረጉት ሸራ ላይ የሚቀቡት በአንድ እጃቸው ብቻ ነው። ይሁንና አንዳንድ በተፈጥሮም ሆነ በአደጋ ሁለት እጃቸውን ያጡ ሰአሊያን በአንድ እጃቸው ብቻ ብሩሽ ወይም እርሳስ መጨበጥ ስለማይችሉ ስዕል ለመሳል ሁለቱንም እጆቻቸውን ይገለገላሉ። ኦዲቲ ሴንትራል ሰሞኑን ከወደ አሜሪካ ይዞት ብቅ ያለው መረጃ ደግሞ ሁለት ጤነኛ እጆችን በአንድ ጊዜ በመጠቀም ስዕል መሳል እንደሚቻል ያረጋግጣል። መክሊት ካልሆነና ከላይ ካልተሰጠ በቀር ስዕልን እንዲሁ በቀላሉ በአንድ እጅ እንኳን ለመሳል ያስቸግራል። በሁለት እጅ በአንድ ጊዜ ሲሆን ደግሞ ጭራሽ የማይታሰብ ይሆናል። ለአሜሪካዊው አማተር ሰአሊ ግን ይህ እጅግ የቀለለ ጉዳይ ነው ይላል የኦዲቲ ሴንትራል ዘገባ። እንደ ዘገባው፤ በአሜሪካ ዴትሮይት ግዛት ጠበቃና አማተር ሰአሊው ኮሊን ዳርክ የተለያዩ ቀለሞችን በመጠቀም ጠለቅ ያሉ የስዕል ጥበብ ስራዎችን በሁለት እጆቹ በአንድ ጊዜ የመስራት ችሎታው ረፍዶም ቢሆን፣ የብዙሃንን ትኩረት ለመሳብ በቅቷል። የ42 አመቱ ይህ ጎልማሳ ከታዋቂ የፊልም አክተሮችና ታዋቂ ሰዎች ጀምሮ የተለያዩ እንስሳትንና ተፈጥሮን የሚያሳዩ ስዕሎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የስዕል ስራዎችን ሁለቱን እጆቹን በአንድ ጊዜ በመጠቀም ለማሳል ብዙ አልከበደውም። ኮሊን ይህን በሁለት እጅ በአንድ ጊዜ የመሳል ጥበቡን ሚስጥር ለረጅም ጊዜ ደብቆ ካቆየው በኋላ በአነቃቂ ንግግር ተነሳስቶ የሚሰራቸውን ስዕሎች የሚያሳዩ ፎቶዎችና የቪዲዮ ክሊፖች በኢንስታግራም መልቀቅ ከጀመረ ወዲህ የብዙሃንን ትኩረት ለመሳብ ችሏል። ‹‹የተደረገልኝ ቀና ድጋፍ የስዕል ስራዎቼን ይበልጥ እንድሰራና ችሎታየን እንድጠቀምበት አነሳስቶኛል››ሲልም ተደምጧል። ‹‹በርግጥ የቀኝ እጄ ሲደክም ስዕል ለመስራት የግራ እጄን እጠቀማለሁም›› ብሏል። በአምስት አመቱ ስዕል መሳል የጀመረው ኮሊን ይህን ችሎታውን በመጠቀም በሆሊውድ ፊልም የሚታወቀውን የሃሪ ፖተር ገፀባህሪ፣ ሊዮናርዶ ዳቪንቺን፣ ኮቤ ብሪያንትንና ሩድ ባድረ የተሰኙ ዝነኞችን ከሰራቸው የስዕል ስራዎቹ ውስጥ ይጠቀሳሉ። በእንዲህ አይነቱ ስዕል የመሳል ጥበብ ኮሊን የመጀመሪያው ሰው እንዳልሆነ ዘገባው ገልጾ፣ከዚህ በፊትም ራጃሴና የተሰኘች ኔዘርላዳዊት በሁለት እጆቿ በአንድ ጊዜ ስዕል እንደምትሰራ መዘገቡን አስታውሷል። የስዕል ስራዎቿ በአንዳንድ ወገኖች የውሸት ናቸው በሚል የተፈረጁ ቢሆንም፣ይህን የሚያረጋግጥ ትክለኛ ማስረጃ ግን እስካሁን እንዳልተገኘ ዘገባው አመልክቷል። አዲስ ዘመን መጋቢት 15/ 2012 አስናቀ ፀጋዬ", "passage_id": "b3d84f41241974feeae15d9a25cca6a3" } ]
99dc3d3af789a79ba305a715bf1b2a2a
21899956b5d85efbc79462ca38c89e30
የዓለም ከዋክብት በቤታቸው ከትመው ልምምዳቸውን ቀጥለዋል
ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪመየር ሊግ አዲስ ውሳኔ ካላስተላለፈ በቀር በተያዘው ወር መጨረሻ ዳግም ወደ ውድድር ለመመለስ ማቀዱ ይታወቃል፡፡ ይህንን ተከትሎም ማንቸስተር ዩናይትድ ከቀናት በኋላ ልምምድ ይጀምራል:: ታዲያ ተጫዋቾች ከአቋማቸው ላለመውረድ በቤታቸው ሆነው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ ማተኮራቸውን በተለያዩ ጊዜያት ለደጋፊዎቻቸው በሚያጋሩት ተንቀሳቃሽ ምስል ያስመለክታሉ፡፡ ይህ ሁኔታም ቀድሞ ለረጅም ሰዓታት አብረዋቸው ያሳልፉ ለነበሩትና አሁን ግን በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች መልዕክት ለሚለዋወጡት አሰልጣኞች መልካም መሆኑን የቀያዮቹ አሰልጣኝ ኦሊጉነር ሶልሻየር ለኢቭኒንግ ስታንዳርድ ገልጸዋል፡፡ ተጫዋቾች ጤናቸውንና አቋማቸውን በመጠበቁ ሂደት ቤተሰቦቻቸውም እንዲያግዟቸው ጭምር ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተዛመተ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ሳቢያ በርካታ ስፖርታዊ ክንዋኔዎች መታገዳቸውን ተከትሎ ስፖርተኞች ከቤታቸው እንዳይወጡ በመከልከላቸው በቤታቸው ሆነው በተለያዩ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲያሳልፉ አስገድዷቸዋል፡፡ በተንቀሳቃሽ ምስል ሁሉም ከገዳዩ ቫይረስ ራሱን እንዲጠብቅ መልእክት በማስተላለፍና ቫይረሱን ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት ድጋፍ ከማድረግ ባለፈም በቤታቸው ውስጥ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በምን መልኩ እንደሚሰሩ ለሌሎች በማስመልከት ላይም ይገኛሉ፡፡ ከተራዘሙ ውድድሮች መካከል አንዱ ኦሊምፒክ እንደመሆኑ በብሄራዊ ቡድን የተካተቱ ስፖርተኞችም ለአንድ ዓመት በምን መልኩ ብቃታቸውን ጠብቀው መቆየት እንደሚችሉ ልምዳቸውን እያካፈሉ ይገኛሉ፡፡ እንግሊዛዊቷ የሁለት ጊዜ የወርልድ ቴኳንዶ የዓለም ቻምፒዮናዋ ጃዴ ጆንስ ለኦሊምፒኩ በተሻለ ብቃት ለመመለስ በአንድ ዓመት መራዘሙን እንደ መልካም አጋጣሚ የምትመለከተው መሆኑን ትገልጻለች፡፡ ውድድሮች፣ የልምምድ አካዳሚዎች እንዲሁም ጂምናዚየሞች በዚህ ወቅት የተዘጉ ቢሆንም በቤት ውስጥ ልምምድ በማድረግ በስፖርቱ የሶስት ጊዜ ቻምፒዮን በመሆን ታሪክ ለመስራት እየተዘጋጀችም ትገኛለች፡፡ ከዚህም ባሻገር ወቅቱን እንደማገገሚያ ጊዜ በመውሰድ ያለመዘናጋት ልምምድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን እንደገለፀች ዘ ጋርዲያን በዘገባው አስነብቧል፡፡ ሌላኛዋ ዋናተኛም በተመሳሳይ የራሷንና የሌሎችን ህይወት አደጋ ላይ ላለመጣል በቤቷ መሆንን አማራጭ የሌለው መሆኑን ታምናለች፡፡ የአምስት ጊዜ ኦሊምፒክ ቻምፒዮናዋ ኬት ሌዴኪ ከሲኤንኤን ጋር በነበራት ቆይታ ከዓመት በኋላ በሚካሄደው ኦሊምፒክ በደካማ አቋም ላለመሳተፍ ልምምዱን በጎረቤቶቿ መዋኛ ገንዳ ላይ አጠናክራ መቀጠሏን ገልጻለች፡፡ በእርግጥ ለ800 ሜትር ነጻ ዋና ቻምፒዮናዋ ልምምድ የምታደርግበት ገንዳ በቂ ባይሆንም ከአቋሟ ዝንፍ ብላ ላለመገኘት ስትል በልምምድ ላይ ትቆያለች፡፡ አንጋፋው ህንዳዊ የስፖርት ጋዜጠኛ ሮሂት ብሪጅናዝ በበኩላቸው ስፖርቱ ሲመለስ የተሻለ ነገር ማግኘት ይሻል ይላሉ፡፡ በቤት ውስጥ መቆየት አስፈላጊ በሆነበት በዚህ ወቅት ውድድሮች ባይኖሩም ከዚህ ቀደም የተካሄዱ ውድድሮችን እንዲሁም ዘጋቢ ፊልሞችን በመመልከት እያሳለፉ መሆኑን ዘ ስቴር ታይምስ አስነብቧል፡፡ በኢትዮጵያም ከዚህ ቫይረስ መስፋትን ተከትሎ ክለቦች፣ ማሰልጠኛ ማዕከላት እንዲሁም ብሄራዊ ቡድኖች ስፖርተኞቻቸውን እንዲበትኑ ተደርጓል:: ስፖርተኞቹ በቡላቸው ባላቸው አቅም ቫይረሱን ለመቆጣጠር በሚደረገው ርብርብ ከደጋፊዎቻቸውና በተናጥል በመሆን ድጋፍ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን ብቃታቸውን ጠብቀው ለመቆየት ምን እያደረጉ እንደሆነ መረዳት አልተቻለም፡፡ ስፖርተኛ ሁሌም ብቁና ዝግጁ ሆኖ መገኘት ያለበት እንደመሆኑ ከሌሎች ተሞክሮ በመውሰድ ይህንን በቤት ውስጥ የማሳለፍ ወቅት አቅማቸው በቻለ መጠን ዝግጅታቸውን ማከናወን ተገቢ መሆኑን የስፖርት ባለሙያዎችም ይመክራሉ፡፡ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ስፖርተኞች በየግላቸው ጊዜውን እንዲያሳልፉና መመሪያዎችን መከተል እንደሚገባቸው በመግለጫው ጠቁሟል፡፡ በሌላ በኩል በአትሌቲክስ ስፖርት የምትታወቀው ኢትዮጵያ አትሌቶች ከአበረታች መድሃኒት የጸዳ ጊዜ ማሳለፍ እንደሚገባቸው ተመልክቷል፡፡ ብሄራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ጽህፈት ቤት አትሌቶች ሳይዘናጉ ራሳቸውን እንዲጠብቁና በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ያልተገባ ጥቅምን ለማግኘት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የህግ ጥሰት በሚፈጽሙት ላይ የእርምት እርምጅ ይወሰዳል፡፡ ከዚህ ቀደም ይከናወን የነበረው የአትሌቶችን ናሙና የመውሰድና የመመርመር ሂደትም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጽህፈት ቤቱ አሳስቧል፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 24/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29639
[ { "passage": "የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማኅበር ሊቀመንበር አቶ አብነት ገ/መስቀል በፊፋ በቀረበላቸው ግብዣ መሰረት የ2018 የሩሲያ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ እና የፍፃሜ ጨዋታዎችን ለመታደም ትላንት ወደ ሩሲያ አቅንተዋል። ትላንት ምሽትም በሴይንት ፒተርስበርግ ስታድየም በመገኝት ፈረንሳይ ከቤልጅየም ያደረጉትን ጨዋታ የተከታተሉ ሲሆን ከዚህ በኋላም ቀሪ ጨዋታዎችን እስከ ፍፃሜው ድረስ በተመሳሳይ መልኩ ጨዋታዎችን ይከታተላሉ ተብሎ ይጠበቃል ።ቅዱስ ጊዮርጊስን በሊቀ መንበርነት የሚመሩት አቶ አብነት ገ/መስቀል በአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌድሬሽን (ካፍ) ውስጥ የክለብ ውድድሮች ኮሚቴ አባል መሆናቸው ይታወቃል።", "passage_id": "3a35a0517f18524fd0e64462ae36906c" }, { "passage": "ከውድድሮች ርቀው በቤታቸው ለሚገኙ ስፖርተኞች ኦንላይን በነፃ የሥነ ልቦና ድጋፍ የማድረግ ዓላማ ያላቸው ባለሙያዎች ዝግጅታቸውን አጠናቀው ወደ ተግባር ሊገቡ ነው።በኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ምክንያት እንደተቀረው ዓለም ሁሉ በሀገራችንም የሊግ እና መሰል ስፖርታዊ ውድድሮች ላልተወሰነ ጊዜ መቋረጣቸው ይታወቃል። በመሆኑም ከለመዱት በእንቅስቃሴ የተሞላ ውሎ በተቃራኒው ተጫዋቾች ጊዜያቸውን በቤታቸው እያሳለፉ ይገኛሉ። በዚህ ሳቢያ ለሚከሰቱ ከአካል ብቃት ጋር ለየገናኙ ችግሮች ክለቦች እና አሰልጣኞች በተለያዩ አማራጮች ተጨዋቾች ብቁ ሆነው ይህን ጊዜ እንዲያሳልፉ ጥረት እንደሚያደርጉ ይሰማል። ከዚህ ባለፈ ግን አዕምሯዊ የሆኑ ጉዳዮች የተዘነጉ ይመስላሉ። ሆኖም ይህን ክፍተት ያስተዋሉ የህክምና ባለሙያዎች በሙያቸው የበጎ ፍቃድ እገዛ ለማድረግ እንዳሰቡ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል።ባለሙያዎቹን በመወከል ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ ያደረጉት ዶ/ር በረከት ፀጋዬ እንደገለፁት\nከዚህ በፊት ያልነበሩ እና የተለዩ እንደ ድብርት ወይም ጭንቀት ዓይነት ስሜቶች የሚሰሟቸው የሙሉ ጊዜ እግር ኳስ ተጨዋቾች ፣ አትሌቶች እንዲሁም ሌሎች ስፖርተኞች የዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ገልፀዋል። ዶ/ር በረከት ችግሩ የሚገጥማቸው ስፖርተኞች ላይ የሚታዩ ምልክቶችን ሲዘረዝሩ ” የተሰጣቸውን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለመተግበር ፍላጎት እና አቅም ማጣት ፣ ለተከታታይ ቀናት/ሳምንታት የድብርት ስሜት ውስጥ መቆየት ፣ የእንቅልፍ መዛባት (ለሊት እንቅልፍ ማጣት እና ቀን መተኛት) ፣ የበዛ ጭንቀት (ስለብዙ ነገሮች ማሰብ) ፣ ተስፋ መቁረጥ እና ከሰዎች ጋር ማውራት ያለመፈለግ ስሜቶች ሊስተዋሉባቸው ይችላል። ” ብለዋል።ህክምናው ለጊዜው ከሦስት እስከ አራት በሚሆኑ የሥነ አዕምሮ ሬዚደንት ሀኪሞች የሚሰጥ ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱም ሲኒየር የሳይካትሪ ሀኪሞች የሚሳተፉበት ይሆናል። ለዚሁ ተግባር ሲባል በተከፈተው የቴሌግራም ግሩፕ ላይ (ሊንኩን ከስር ማግኘት ይችላሉ) መሰል ችግሮች ያሉባቸው ስፖርተኞች የህክምና ባለሙያዎቹን ማግኘት ይችላሉ። ሀኪሞቹም ዘወትር ረቡዕ ምሽት ከ11:00 – 01:00 እንዲሁም እሁድ ጠዋት ከ05 ፡00 – 07:ዐዐ ድረስ በቴሌግራም ግሩፑ ላይ ኦንላይን ሆነው የሚጠባበቁ ሲሆን ህክምናውንም ኦንላይን ወይንም በስልክ በኩል ከዛም አለፍ የሚል ከሆነ በአካል በመገናኘት በበጎ ፍቃደኝነት የሚሰጡ ይሆናል። ሆኖም አሁን ካለው ሁኔታ አንፃር ስፖርተኞችንም ከወጪ ለመከላከል አብዛኛው እገዛ በኦንላይን እና በስልክ እንዲያቅ ለማድረግ እንደሚጥሩም ዶ/ር በረከት ገልፀውልናል። ከዚህ በተጨማሪ የዶክተሮቹ ስብስብ በቀጣይ ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር ጋር በቅርበት የመስራት ሀሳብ እንዳለው ተናግረዋል።መሰል እገዛ ማግኘት የምትፈልጉ ስፖርተኞች ይህን ሊንክ በመጠቀም ወደ ቴሌግራም ግሩፑ መቀላቀል ትችላላችሁ።  👉  ", "passage_id": "7e73cabfaa8be67a612e3e6c9d723803" }, { "passage": "ዓለምን በአንድነት እያስጨነቀ የሚገኘው ወቅታዊ ጉዳይ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ወረርሽኝ መሆኑ ይታወቃል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ያስቻለ ፈውስ በዓለም ሳይንቲስቶች፣ የህክምና ጠቢባንም ይሁን በሃያላን አገራት አቅም ማምጣት አልተቻለም። ይህም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ከመለወጥ አንስቶ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በርካታ አሉታዊ ተፅዕኖው እንዲያርፍ አድርጓል። የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ተጽዕኖ እያስተናገደ ከመሆኑ ባሻገር፤ ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጉን መረጃዎች ያመላክታሉ። በወረርሽኙ ሳቢያ ትልልቅ የስፖርት ውድድሮች በመራዘማቸው፣ በመሰረዛቸው እና በመስተጓጐላቸው ኢንዱስትሪውን ከፍተኛ ገቢ እንደሚያሳጣው የተለያዩ ትንበያዎች አመልክተዋል። \nየስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰ ርሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል፡፡ በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በዚህ ዓመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል። የስፖርት እንቅስቃሴን ጨምሮ ሌሎች መደበኛ እንቅስቃሴዎችን በቅርብ ጊዜ ማድረግ የሚቻልበት ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ምልክቶች እየታዩ አለመሆኑ፤ በኢንደስትሪው ላይ የሚደርሰው ቀውስ እንዲያሻቅብ እንደሚያደርገው ተነግሯል። \nየቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ በመሆኑ ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ጠባብ መሆኑ እየተነገረ ባለበት ወቅት ቢቢሲ ከቀናት በፊት ይዞት የወጣው መረጃ ተስፋ ሰጪ ሆኗል። ቢቢሲ ፤ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን\n የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር ሊመለሱ መሆኑን ጽፏል። ከዚህ ውስጥ ደግሞ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ግንባር ቀደም ሊሆን እንደሚችል አስነብቧል። የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ ማሳባቸውን ጠቅሶ፤ በተለይ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማጠናቀቅ ቆርጠው ተነስተዋል ሲል አስነብቧል። \nየዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን መለገሳቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ የተለያዩ ሀገራት ሊጎች እንደ አማራጭ እየቀረበ ይገኛል። በዝግ ስታዲየም ውድድሮችን አማራጭን ወደ ተግባር ለመቀየር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ቆርጠው መነሳታቸውን አስነብቧል። \nየ2020 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር የተቋረጠው። ሊጉ የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ 92 ጨዋታዎች ይቀሩታል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም የውድድር ዘመኑን በመደበኛው መልኩ ለማካሄድ ለመመለስ የሚያስችል ተስፋ የለም። የ2020 ውድድር ዘመን 92 ጨዋታዎችን እንዴት እናጠናቅ በሚለው ዙሪያ የሊጉ ክለቦች የቪድዮ ስብሰባ አድርገዋል። \nበስብሰባው ላይ እንደ ሕክምና ባለሙያዎች ያሉ ያገባቸዋል የተባሉ ሰዎችም ተገኝተው ነበር። ክለቦች ሊጉ በቀላሉ ወደ ውድድር እንደማይመለስ መግባባት ላይ ደርሰዋል። የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ የተቀሩትን ውድድሮች በዝግ ስታዲየም ለማድረግ ከስምምነት መድረሳቸውን ቢቢሲ አስነብቧል። በቪዲዮ ስብሰባ ወቅት «የሊጉ ክለቦች ይህን ለማድረግ ደግሞ ቢያንስ 10 ገለልተኛ ሜዳዎች ያስፈልጋሉ ። ገለልተኛ\n ሜዳዎችን መጠቀም ያስፈለገው ደጋፊዎች ከሜዳ ውጪም ቢሆን እንዳይሰበሰቡ በማሰብ ነው። አልፎም የሚመረጡት ሜዳዎች ከፖሊስና የስፖርት ሜዳዎችን ደህንነት ከሚመረምር አካል ይሁንታ ያገኙ መሆን አለባቸው» መባሉን በዘገባው አስፍሯል። በተጨማሪም ተጫዋቾች በሳምንት ሁለት ጊዜ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ይደርግላቸዋል። በየቀኑ ደግሞ የበሽታው ምልክት ታየባቸው አልታየባቸው የሚለው ይለካል። አልፎም ሜዳዎች በየጊዜው ንፅህናቸው ይጣራል ተብሏል። ተጫዋቾች ከጨዋታ ውጪ ባሉት ጊዜያት ሁሉ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አለባቸው። በውድድር ስፍራዎች ውስጥም ምግብ መብላትም ሆነ ገላን መታጠብ እንዳይችሉ የሚደረግ መሆኑን አመልክቷል። \nየእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማ ጠናቀቅ በገለልተኛ ሜዳ ውድድሮችን ለማድረግ ከስምምነት መድረስ ቢችሉም ከሀገሪቱ መንግስት በኩል የሚኖረውን ተቀባይነት ምን ሊሆን ይችላል ? የሚለው ምላሽ የሚያሻ መሆኑን ዘገባው አንስቷል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት እንዲቆም የተደረገው። የፕሪሚየር ሊጉ አስተዳዳሪ አካል መንግሥት ይሁንታ ሲሰጥ ብቻ ወደ ሜዳ የሚመለስ መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። \nየውድድር አመቱ የቀሩትን 92 ጨዋታዎች ለመጫወት ከስምምነት ቢደርሱም የሀገሪቱ መንግስት ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል የተባለ ነገር አለመኖሩን ዘገባው ጠቅሷል። የዚህ ዓመት ወድድር ይቋረጥ የሚል ሐሳብ ከየትኛውም ክለብ አልመጣም ነበር። በመሆኑም በሁሉም የሊጉ ክለቦች በኩል የተወሰነው ውሳኔ ከመንግስት ድጋፍ የሚያገኝ ከሆነ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መቋጫው በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ሊሆን እንደሚችል ግምቱን አስፍሯል። የእንግሊዝ መንግሥት እንቅስቃሴዎች ቀስ በቀስ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ካደረገ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በዝግ ሜዳ ወደ ውድድር እንደሚመለስ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 27/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "35430572a053b74df06f2fa400489660" }, { "passage": "በፊፋ የ2018 ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ፈረንሳይ እና ዩራጋይ ዓርብ ይጫወታሉ፡፡ በዚህ ጨዋታ ላይ የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮ በፓሪስ እና አቅሪቢያዋ ከተወጣጡ ታዳጊ እግርኳስ ተጨዋቾች ጋር ይህንን የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ለመመልከት አቅደዋል፡፡ ከተጋበዙ ተጨዋቾች መካከል ደግሞ ከኢትዮጵያዊያን ቤተሰቦች የተወለደው ብሩክ ሲሳይ ይገኝበታል፡፡እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በየካቲት 2/2005 በፓሪስ አቅራቢያ የተወለደው ብሩክ በቡሎኝ ቢዮንኩር ክለብ ውስጥ በአጥቂነት እየተጫወት ይገኛል፡፡ የ13 ዓመቱ ቡሩክ ፕሬዝደንት ማክሮ በዓለም ዋንጫው ፈረንሳይ ከዩራጋይ የሚደርጉትን ጨዋታ በኤሊዜ ቤተ-መንግስት እንዲመለከት ጥሪ ከቀረበለት ተስፈኛ ታዳጊዎች መካከል አንዱ ሲሆን ተጨዋቹ እና አባቱ አቶ ሲሳይ መሃቤ እድሉን አግኝቶ ፕሬዝደንት ማክሮን የማግኘት እና የዓለም ዋንጫ ጨዋታን የመመልከት እድል በማግኘቱ ደስተኛ መሆናቸው ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ቡሎኝ ቢዮንኩር በተለያዩ ስፖርቶች የሚሳተፍ በፓሪስ አቅራቢያ የሚገኝ ክለብ ሲሆን በእግርኳሱ በይበልጥ ለወቅቱ የፈረንሳይ ሃያል ክለብ ፓሪ ሰ ዠርማ መጋቢ በመሆን ይታወቃል፡፡ በክለቡ ውስጥ አልፈው ትልቅ ደረጃ ሊደርሱ ከቻሉ ተጨዋቾች መካከል የቀድሞ የኒውካስል ዩናይትድ የክንፍ ተጨዋች ሃቲም ቤን አርፋ እና የቀድሞ የሊቮርኖ እና ፓርማ አጥቂ አልጄሪያዊው ኤሻክ ቤልፎዲል ይጠቀሳሉ፡፡ብሩክ በመጪው ሰኞ በስዊድን በሚዘጋጀው ጎቲያ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ከክለቡ ጋር ወደ ጎተንበርግ ያመራል፡፡ ጎቲያ ዋንጫ በዓለማችን በርካታ ቁጥር ያላቸውን የታዳጊ ቡድኖች በማሳተፍ የሚስተካከለው ውድድር የለም፡፡ የስዊድኑ ክለብ ቢኬ ሃከን በሚዘጋጀው በዚህ ውድድር ላይ ከዚህ ቀድም አሁን በህይወት በሌለው የቀድሞ ድንቅ አጥቂ አሰግድ ተስፋዬ የሚመራው አሴጋ የእግርኳስ አካዳሚ መሳተፉ ይታወሳል፡፡", "passage_id": "17a7a54235f9f268953c3e1cfa3aa1a8" }, { "passage": " የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ልዑካን ቡድን በሀገር ውስጥ ዝግጅቱን አጠናቅቆ ትናንት ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ገብቷል። በትናንትናው እለትም በአዛም ኮምፕሌክስ ሜዳ ተመሳሳይነት ባለው የሰው ሰራሽ ሜዳ አንድ ሰዓት ከ30 ደቂቃ የቆየ ልምምዳቸውን በመስራት በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቃቸው ታውቋል። የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ በመሆን በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ውድድር ተሳታፊ ሆኖ የመጀመሪያውን የማጣሪያ ጨዋታ በሜዳው የባህርዳር አለም አቀፍ ስታዲየም አዛምን 1ለ0 ማሸነፉ ይታወሳል። ክለቡ የፊታችን እሁድ ነሃሴ 18 ቀን በአዛም ኮምፕሌክስ ስታዲየም የመልሱን ጨዋታ ለማከናወን በባህርዳር እና በአዲስ አበባ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ዝግጅት በማድረግ በሀገር ውስጥ የመጨረሻ ልምምዳቸውን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከትናንት በስቲያ በመስራት ነበር በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቃቸው የተገለጸው። በአፄዎቹ የቡድን ስብስብ ቀደም ብሎ\nጉዳት የደረሰበት አብዱራህማን ሙባረክ (ግሪዳው) በህክምና ላይ የሚገኝ ሲሆን ከአዛም ጋር የማሸነፊያዋን አንድ ጎል ያስቆጠረው\nበዛብህ መለዮ በጉዳት ሁለት ቀን ልምምዱን ያልሰራ ሲሆን በጨዋታው ላይ ጉዳት አጋጥሞት ከሜዳ የወጣው ሚካኤል ሳማኪ ከጉዳቱ አገግሞ\nልምምዱን በመስራት ላይ ይገኛል። “ክለባችንን አዲስ የተቀላቀሉት እንየው ካሳሁን እና ኪሩቤል ሃይሉን ጨምሮ ሌሎች ሁሉም ተጫዋቾች\nበሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ” ሲል ክለቡ በመረጃው አስታውቋል። አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከክለቡ ጋር\nመለያየታቸውን ተከትሎ አዲሱ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ከምክትል አሰልጣኞቻቸው እና ከሙሉ የኮችንግ ስታፉቸው ጋር በመሆን በታንዛኒያ\nዳሬ ሰላም ከአዛም ጋር ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ ትኩረት በማድረግ ክለቡ አሸንፎ ወደ ቀጣይ ዙር እንዲያልፍ የተሳካ ዝግጅት ማድረጋቸውም\nተገልጿል። የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ልዑካን በትናንትናው እለት ማለትም ነሃሴ 15 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ\n2 ሰዓት ከአዲስ አበባ ቦሌ አለምአቀፍ ኤርፖርት ወደ ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም መጓዙም ለማወቅ ተችሏል ። በተመሳሳይ በርካታ ደጋፊዎች\nአርብ ነሃሴ 17 ቀን ክለባቸውን ለመደገፍ ወደ ስፍራው እንደሚጓዙ ክለቡ በመረጃው አስፍሯል። በተመሳሳይ በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፈው መቐለ ሰብዓ እንደርታ የማጣሪያ\nየመልስ ጨዋታውን እሁድ ነሐሴ 19 ቀን 2011 ዓ.ም በመቐለ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ከኢኳቶሪያል ጊኒው ክለብ ካኖ ስፖርት አካዳሚ\nጋር ያደርጋል። ነሐሴ 4 ቀን ዓ.ም በተደረገው የመጀመሪያ ጨዋታ ካኖ ስፖርት አካዳሚ በጆሴ ፔድሮ ኦቢያንግና ጆሴ ፊደል ሲፒ ጎሎች\nመቐለ ሰብዓ እንደርታን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የ2011 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው መቐለ 70 እንደርታ በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ኢትዮጵያን\nየወከለ ክለብ እንደመሆኑ፤ በሜዳው ለሚያደርገው ጨዋታ ትልቅ ግምት ሰጥቶ እንደሚጫወት ይጠበቃል። በአሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ\nየሚመራው መቐለ 70 እንደርታ ከ15 ቀናት በፊት 2 ለ 1 በሆነ በጠባብ የግብ ክፍያ የደረሰበትን ሽንፈት በማካካስ ውጤቱን ለመቀልበስ\nትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱ ተገልጿል። በአሁኑ\nወቅት ያሬድ ከበደ በጉዳት ምክንያት ከጨዋታ ውጪ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ፤ ከያሬድ በስተቀር ሁሉም ተጫዋቾች በመልካም ጤንነትና\nአቋም ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል። ሁለገብ ተጫዋች እንደሆነ የሚነገርለት ያሬድ በተለይ በመጀመሪያው ጨዋታ ወቅት ጥሩ እንቅስቃሴ\nበማድረግ ረገድ አይነ ገብ እንደነበር በመጥቀስ የተጫዋቹ መጎዳት ክለቡን ሊጎዳው እንደሚችል በስጋት እየተነሳ ይገኛል።አዲስ ዘመን ነሀሴ 17/2011 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "117bcb0b93cb46d13710d3a15d4db78f" } ]
1e333a1335059e26246ee3d6bd623ec7
8f680d87be747024b1d0fe7df4aa9015
የዊምብልደን ፈተና ከ2ኛው የዓለም ጦርነት እስከ ኮቪድ- 19
እኤአ ታኅሣሥ 31 ቀን 2019 በቻይና ዉሃን ግዛት የኮሮና ቫይረስ እንደተከሰተ የዓለም የጤና ድርጅት ማስታወቁን ተከትሎ የቻይና መንግሥት በአፋጣኝ የቫይረሱን ስርጭት በአጭሩ ለመቅጨት እርምጃ ወደ መውሰድ ገብቶ ነበር። የቫይረሱን ስርጭት እንደተባለው በቀላሉ ለመቆጣጠር ሳይቻል ቀርቷል። አሁንም ቢሆን በዓለም አራቱም አቅጣጫዎች የተሰራጨውን ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ያስቻለ ፈውስ በዓለም ሳይንቲስቶች፣ የህክምና ጠቢባንም ይሁን በሀያላን አገራት አቅም ማምጣት አልተቻለም። ይህም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ከመለወጥ አንስቶ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በርካታ አሉታዊ ተፅዕኖው እንዲያርፍ አድርጓል፡፡ የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ተጽእኖ እያስተናገደ ከመሆኑ ባሻገር፤ ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጉን መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ የኮሮና ቫይረስ ለዓለም ራስ ምታት እንደሆነ በመቀጠሉ የስፖርቱ እንቅስቃሴ ዛሬም መፈተኑን ቀጥሏል። ስፖርታዊ ክንውኖች ለማድረግ አስቸጋሪ የመሆኑን ያህል በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ግምት ያለውን ኦሊምፒክ ጨዋታ እንዲራዘም ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ከሳምንት በፊት የ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ በምንም አይነት ሁኔታ ይካሄዳል የሚል አቋም የነበረ ቢሆንም በተቃራኒው ውሳኔ እንዲተላለፍ የቫይረሱ ስርጭት አስገድዷል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስፖርትን መፈተኑን እንደሚቀጥልም የቢቢሲ ዘገባ ያመለክታል። የዓለም ህዝብ የጋራ ስጋት በሆነው የኮቪድ -19 ወረርሽኝ በስፖርቱ ላይ እየደረሰ የሚገኘው ተጽእኖ እየጨመረ ይገኛል። በእንግሊዝ ዊምብልደን ላይ የሚደረገው እና የዓለማችንን ሥመጥር የሜዳ ቴኒስ ተጫዋቾች የሚያሳትፈው ታላቅ ውድድር እንዲሰረዝ ውሳኔ ተደርሷል። በዓለም ዓቀፍ ደረጃ እጅግ ተጠባቂ የሆነው ውድድር ለመሰረዙ የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ሆኗል። የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የስፖርቱን ገጽታን ምንኛ እየጎዳው እንደሚገኝ ይህ ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ዘገባው ያትታል፡፡ ዘጋርዲያን ደግሞ፤ በእንግሊዝ ዊምብልደን ላይ የሚደረገው እና የዓለማችንን ሥመጥር የሜዳ ቴኒስ ተጫዋቾችን የሚያሳትፈው ውድድር ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተሰረዘ ጽፏል። የዊምብልደን ቻምፒዮና የተቋረጠው እኤአ ከ1940 እስከ 1935 ድረስ የዘለቀው የሁለተኛው ዓለም ጦርነት እንደነበር አስታውሷል። በዚህ ጦርነት መጨረሻ የአክሲስ ሃያላት ማለትም ጀርመን፣ ጣልያንና ጃፓን ተሸነፉ። እኤአ ታህሣሥ 2019 በተነሳው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት የ134ኛ ዊምብልደን ቻምፒዮና ተመሳሳይ እጣ ፈንታ ሊደርሰው እንደቻለ ዘገባው ተመልክቷል። የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ስፖርታዊ ክንውን ለማድረግ ፈታኝ እንደሆነው ሁሉ በአሁኑ ወቅት የኮሮና ቫይረስ የዓለምን ህዝብ እያሸበረ መሆኑን ተከትሎ ቻምፒዮናውን በተያዘለት መርሃ ግብር ለማካሄድ እንዳይቻል አድርጎታል።በዚሁ መሰረት ለሁለት ሳምንታት የሚካሄደው ይህ ስፖርታዊ ውድድር በሜዳ ቴኒስ ስፖርት አፍቃሪያንና ተወዳዳሪዎች ዘንድ ትልቅ ስፍራ ነበረው። ውድድሩ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው በሐምሌ ወር መጀመሪያ እንደነበር ታውቋል። በዩናይትድ ኪንግደም እስከ ሐምሌ ወር መጨረሻ ድረስ አንድም የቴኒስ ጨዋታ እንዳይካሄድም ውሳኔ ተላልፏል፡፡ ዘጋርዲያን 134ኛው የዊምብልደን ቴኒስ ቻምፒዮና መርሃ ግበር መሰረዙን ተከትሎ የዓለማችን እውቅ ተጫዋቾች ልብ እንደ ደማ ዘግቧል። የዊምብልደን የ8 ጊዜ ቻምፒዮናው ሮጀር ፌደረር ለዚህ ታላቅ መድረክ ባለፉት ሁለት ወራት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደረግ ነበር። ‹‹በቻምፒዮናው ላይ አዲስ ውጤት ለማስመዝገብ የነበረንን ተነሳሽነት ጨምሮ ሁሉም ነገር ተበላሽቷል» ሲል መከፋቱን ፌደረር ገልጿል። ሰሬና ዊሊያምስ በተመሳሳይ «የተሰማው ዜና እጅግ አስደንጋጭ ነው» ስትል የቻምፒዮናው መራዘም በስፖርቱ ቤተሰብ ላይ ሀዘን እንደፈጠረ ተናግራለች። ዶቼቬሌ በበኩሉ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት የስፖርቱን እንቅስቃሴና ገቢ ክፉኛ መጉዳቱን እንደቀጠለ ዘግቧል። ቶኪዮ-ጃፓን ሊደረግ ታቅዶ የነበረው የዘንድሮው ኦሊምፒክ በኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ወደ መጪው ዓመት እንደተራዘመው ሁሉ የዊምብልደን ውድድር መራዘሙ ትልቅ ሀዘን የፈጠረ ውሳኔ መሆኑን አመልክቷል። የቫይረሱን ስርጭት ተከትሎ በየአገሩ የተለያዩ የስፖርት ውድድሮች ተቋርጠዋል። ክለቦች፣ ተጫዋቾች፣ቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ የስፖርት ጋዜጠኞችና ሌሎችም ገቢ ማጣታቸውን እያስታወቁም ይገኛል። በዚህ ወቅት የዌምብልደን ቻምፒዮና መሰረዙ በስፖርቱ ላይ ተጨማሪ ድብርትን የሚፈጥር መሆኑን አመልክቷል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭቱ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን ተከትሎ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ አደጋ እየጣለ መምጣቱን ዛሬም መቀጠሉን ተከትሎ በስፖርቱ ዘርፍ ላይ የማይሻር ጠባሳ እንዲያርፍ ማድረጉን ዘግቧል። አዲስ ዘመን መጋቢት 25/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29701
[ { "passage": "በርኒ ሳንደርስ በሚሽጋን ማሸነፋቸው የዲሞክራስያዊ ፓርቲን ውክልና አግኝቶ ለሀገሪቱ ፕረዚዳንትነት ለመወዳደር በዲሞክራቶች መካከል የሚካሄደው ውድድር እንደሚቀጥል አመላክቷል። እስካሁን ባለው ጊዜ ቀዳሚ ቦታ የያዙት ክሊንተን መሆናቸው ይታወቃል።“የዛሬው ሁኔታ የሚያሳየው የበርኒ ሳንደርስ የምርጫ ዘመቻ፣ እየተነጋገርንበት ያለነው ህዝባዊ አብዮት፣ እያወራንበት ያለለነው ፖለቲካዊ አብዮት በያንዳንዱ የሀገሪቱ ክፍል ጠንካራ መሆኑን ነው።” ብለዋል ሳንደርስ። ሂለሪ ክሊንተን በሚሲሲፒ በብዙ ድምጽ አሸንፈዋል። በሚሽጋንም የተወካዮችን ድጋፍ ከሳንደርስ ይጋራሉ። በመጪው ሳምንት በአምስት ትልልቅ ክፍለ-ግዛቶች በሚካሄደው ቀዳሚ ምርጫም በተወካዮች ውክልና ረገድ በሰፌው እየመሩ ነው። \"ለኔ ከሰራችሁ እኔን ከመረጣችሁ ለናንተ እለፋለሁ። በእያንዳንዷ እለት ጠንክሬ እሰራለሁ።” ይላሉ ክሊንተን። በሪፓብሊካውያን በኩል ዶናልድ ትራምፕ በሚሲሲፒና በሚችጋን በማሸነፋቸው የሪፑብሊካዊው ፓርቲ ውክልና ወደ ማግኘት የሚያመራቸው አንድ እርምጃ ሄደዋል።ትራምፕ በበኩላቸው ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ በሳቸው ላይ አሉታዊ የሆኑ ማስታወቅያዎች በቴሌቪዥን ሲታዩ የቆዩ ቢሆንም በማሸነፋቸው ኩራት እንደተሰማቸው ገልጸዋል።“ክፉኛ አጥቅተውኛል። እያንዳንዳቸው ያጠቁኝ ስዎችም ሄደዋል። ለዚህም ኩራት ይሰማኛል። በሀገራችን መኖር ያለበት ይህ ነውና።”ብለዋል ትራምፕ። የኦሃዮ ክፍለ-ግዛት አስተዳዳሪ ጆን ኬሲችና ሴኔተር ቴድ ክሩዝ ወደ ኋላ ቀርተዋል። ኬሲች ደጋፊዎቻቸው በመጪው ሳምንት በክፍለ-ግዛታቸው ወደ ሚካሄደው ቀዳሚ ምርጫ አሻግረው እንዲያዩ አሳሳበዋል።“ሰዎች በአዎንታዊ መንፈስ የሚካሄድ የምርጫ ዘመቻን መሸለም የጀመሩ ይመስለኛል። በፖለቲካው አለም ማድረግ ያለባችሁ ይህን ነው በማለት ልጆቻቸውን የሚያስተምሩበት። ለአንድ ሳምንት ጠብቁና በኦሃዮ ክፍለ-ግዛት እናሸንፋለን እናም ሁኔታዎች ይለወጣሉ።”ሲሉ ገልጸዋል ኬሲች።በአይዳሆው ቀዳሚ ምርጫ ያሸነፉት ቴድ ክሩዝ ትራምፕ በብሄራዊ ደረጃ ያላቸው ድጋፍ እየወረደ መሆኑን የድምጽ መለክያ አሀዞች መግለጻቸውን ሳይጠቅሱ አላለፉም።“ከዶናልድ ትራምፕ ጋር ትንንቅ ላይ መሆናችንን የሚያሳዩ አሃዞች ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ዎል ስትሪት ጆርናል ላይ እንደወጡ እናውቃለን።”ብለዋል ቴድ ክሩዝ። በመጪው ሳምንት ማክሰኞ ላይ ቀዳሚ ምርጫ ከሚካሄድባቸው አምስት ክፍለ-ግዛቶች ዋናዎቹ ፍሎሪዳና ኦሃዮ ናቸው።የአሜሪካ ድምፅ ብሄራዊ ዘጋቢ ጆም ማሎን የትላንቱን ቅድመ-ምርጫ አጠቃላይ ውጤት አጠናቅሯል። አዳነች ፍሰሀየ ታቀርበዋለች። ", "passage_id": "a5ea9db141c2fbbcea6583334fc26b7a" }, { "passage": "ጭር ያሉት የኮፐንሃገን ጉዳናዎች\n\nይህን ለማድረግ ከአውሮፓ አገሮች ቀዳሚዋ ናት።\n\nዴንማርክ ከወራት በፊት ወረርሽኙ ሲጀማምር ሰሞን ትምህርት ቤቶችንም ሆነ የንግድ ተቋማትን ለመዝጋት ከቀዳሚ አገራት ተርታ ነበረች።\n\n\"ከሚያስፈልገን ጊዜ በላይ በራችንን መዝጋት ያለብን አይመስለንም\" ብለዋል ክብርት ጠቅላይ ሚኒስትር ሜት ፍሬድሪክሰን።\n\nከሞላ ጎደል የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በዴንማርክ በቁጥጥር ሼር የዋለ ይመስላል። መንግሥት የአገሪቱን ምጣኔ ሀብት እንደገና ማንቀሳቀስ ይፈልጋል።\n\nዴንማርክ እየወሰደችው ያለው እርምጃ ግን ግብታዊ የሚባል አይደለም። በከፍተኛ ጥንቃቄ እየሆነ ያለ ነው። ንግዶችና ሌሎች እንቅስቃሴዎች እየተከፈቱ የሚመጡትም ቀስ በቀስ ነው።\n\nጠቅላይ ሚኒስትሯ ፍሪድሪክሰን እንዳሉት ነገሩ በቀጭን ገመድ ሚዛንን ጠብቆ እንደመራመድ ያለ ነው።\n\n\"ሁሉንም ነገር በአንድ ጊዜ ከከፈትነው፣ ወረርሽኙ በአንድ ጊዜ ሰማይ ይነካል፤ ያን ጊዜ በድጋሚ ለመዝጋት እንገደዳለን\" ብለዋል።\n\nሆኖም ዴንማርክ ድንበሮቿ ዝግ እንደሆኑ ይቆያሉ።\n\nጠቅላይ ሚኒስትር ሜት ፍሬድሪክሰን\n\nከዴንማርክ ሌላ የትኞቹ አገራት በራቸውን እየከፈቱ ነው?\n\nኖርዌይና ኦስትሪያም የዴንማርክን ፈለግ እየተከተሉ ነው። ቀስ በቀስ በራቸውን በትንሹ መክፈት ይዘዋል።\n\nኦስትሪያ እንዲያውም ዛሬ ማክሰኞ ሱቆችን ከፋፍታለች። ሆቴሎችና ሬስቶራንቶችም ቀስ በቀስ እየተከፈቱ ነው።\n\nኖርዌይ ከ6 ቀናት በኋላ በኤፕሪል 20፣ የመዋዕለ ሕጻናትና አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ ትፈቅዳለች።\n\nቡልጋሪያ የገበሬዎች እርሻ እንዲከፈት ፈቅዳለች። በቼክ ሪፐብሊክ ደግሞ መናፈሻዎች ተከፍተዋል። የሕንጻ መሣሪያ መደብሮች ወደ ሼል ተመልሰዋል።\n\nበኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ክፉኛ የተመሰቃቀለችው ስፔንም ከሰኞ ጀምሮ አንዳንድ እንቅስቃሴዎቿ ወደነበሩበት ይመለሳሉ ተብሏል። ዜጎች የአፍ-አፍንጫ ጭምብል በየአውቶቡስ ተራና ባቡር ጣቢያ ይታደላቸዋል ተብሏል።\n\nከነዚህ የአውሮፓ አገራት ውጭ ያሉት ግን ከወረርሽኙ በፊት የነበረውን እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል ወደነበረበት ለመመለሾ ጊዜው ገና ነው ብለው ያምናሉ። \n\nየዩናይትድ ኪንግደም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶሚኒክ ራብ \"እንዲህ ዓይነቱን ነገር ለማሰብ የምንሞክርበት ወቅት ላይ አይደለንም\" ብለዋል።\n\nዴንማርክ ለምን ቸኮለች ታዲያ? \n\nከሌሎች የአውሮፓ አገሮች ጋር ሲነጻጸር ዴንማርክ እግዱን በመጣሉም ሆነ በማንሳቱ ቀዳሚ ናት ብለናል። ለምሳሌ የመጀመርያውን እግድ የጣለችው ከዩናይትድ ኪንግደም በሁለት ሳምንት ቀድማ በማርች 11 አካባቢ ነበር።\n\nያን ጊዜ ዴንማርክ ከ10 ሰው በላይ በአንድ ቦታ እንዳይሰባሰብ፣ ሠራተኞች ወደ ሼል እንዳይሄዱ፣ ድንበሮችም እንዲዘጉ ነበር የወሰነችው።\n\nይህ ግን ከጎረቤቷ ስዊድን ፍጹም የተለየ ውሳኔ ነበር። \n\nበስዊድን ብዙዎቹ ነገሮች ከወረርሽኙ በፊት እንደነበሩ ነው ያሉት ማለት ይቻላል። በቅርቡ ብቻ ከ500 ሰዎች በላይ መሰብሰብ የሚከለክለውን ደንብ ወደ 50 ዝቅ አድርጋለች።\n\nነገር ግን የዴንማርክን የወረርሽኝ ጊዜ ደንብ ከነፈረንሳይና ጣሊያን እንዲሁም ዩናይትድ ኪንግደም ጋር ካስተያየነው እጅግ የላላ ሆኖ እናገኘዋለን።\n\nለምሳሌ ዴንማርክ ቤት ውስጥ ቆልፋችሁ ዋሉ የሚል ደንብ አልነበራትም። ቡና ቤቶች፣ ስፖርት ቤቶችና ጸጉር ቤቶች ዝግ እንዲሆኑ ብታዝም አነስተኛ ሱቆች ዝግ እንዲሆኑ ግን አልደነገገችም።\n\nየጤና ስታትስቲክስ ቁጥሮች እንደሚጠቁሙት ከሆነ ዴንማርክ ከብዙ የአውሮፓ አገሮች በአንጻራዊነት ልል የነበሩ ድንጋጌዎቿ ጎድቷታል ብሎ መደምደም ይከብዳል።\n\nእስከ ሰሞኑ ድረስ ዴንማርክ የሞቱባት 260 ሰዎች ብቻ ናቸው። ተያዙ የተባሉት ሰዎች ቁጥርም 6 ሺህ አካባቢ... ", "passage_id": "4f114b539bfe5ce6521ed22a564fb0eb" }, { "passage": "ቶክዮ የ2020 ኦሎምፒክ ውድድሮችን ለማከናወን ሁሉን አሰናድታ ዝግጅቷን ማልዳ ብትጨርስም፣ እንደ እንግዳ ደራሽ የሆነው ኮቪድ 19 ኮሮና ቫይረስ በመጨረሻው ሰዓት ድግሷን እንዳይሆን አድርጎታል። ይህም ብቻ አይደለም፣ ለውድድሩ ራሳቸውን በሚገባ እያዘጋጁ የነበሩ፣ ለድልም መንፈሳቸውን ያበረቱ አትሌቶችን ምኞትና ፍላጎት አደብዝዟል። ምንም እንኳ በ2021 ውድድሮች መካሄዳቸው አይቀርም ቢባልም፣ በአስጊነት ማማ ላይ የተቀመጠው ወረርሽኙ በቀጣይ ዓመትስ እንደማይኖር፣ እንደሚጠፋ ምን ዋስትና አለ እየተባለ ነው።ታድያ የወረርሽኙ ስጋት አስቀድሞ ባጠላባቸው አውሮፓ አገራት እግር ኳሱም ተመሳሳይ እጣ ነው የገጠመው። ሁሉም በሚባል ደረጃ ጨዋታዎች የተቋረጡ ሲሆን፣ እስከ ቅርብ ጊዜም ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝመው ነበር። ውድድሮቹ የሚቋረጡ ከሆነ የዓመቱ አሸናፊ ማን ይሆናል? ከታችኛው ከሚባለው ምድብ (ዲቪዚዮን) የሚገኙና ለማደግ ብዙ ወጪ አውጥተው ዓመቱን የተጫወቱ፣ በሊጉ ደግሞ ባላቸው ዝቅተኛ ነጥብ ወደ ታችኛው ምድብ የሚወርዱና መሰል ኹነቶች በቫይረሱ ምክንያት ተዛብተዋል።ታድያ ውድድሮች የሚሰረዙ ከሆነ ዓመቱ እንዳልነበረ ሙሉ ለሙሉ የማጥፋት ያህል የሚቆጠር ነው፣ ለእግር ኳስ ቤተሰብ። ይህ እንዳይሆንም ብዙ ሙግትና ክርክሮች የተካሄዱ ሲሆን፣ የአውሮፓ እግር ኳስ እንቅስቃሴ የጀመረ ይመስላል። የጀርመን ቡንደስ ሊጋም በዚህ ቀዳሚውን እርምጃ ወስዷል። ከኹለት ወር በኋላ በዘመነ ኮሮና የመጀመሪያውን የእግር ኳስ ጨዋታ በዝግ ስታድየም አካሂዷል። ቦርስያ ዶርትሙንድ እና ሻልካ ባደረጉት በዚህ ጨዋታም ዶርትሙንድ አራት ለባዶ አሸንፏል። ደስታው ግን እንደ ወትሮው አይደለም።ይህን በሚመለከት ከቀናት በፊት አልጀዚራ ባስነበበው ዘገባ፣ የጀርመኑ ሊግ ውድድር ይጀምር እንጂ የቀደመ መልኩ ጠፍቷል። ተጫዋቾች ለብቻቸው እንጂ አብረዋቸው ወደ ሜዳ የገቡ ሕጻናት ልጆች የሉም፣ መነካካት አይታሰብም፣ ከዳኞች ጋር መጨባበጥም እንደዛው፣ ጎል አግብቶ መተቃቀፍ ቀርቷል። ጨዋታው ሲደረግ ከክለቦቹ አስፈላጊ ሰዎች፣ እሳት አደጋ ሠራተኞችና ጥቂት ፖሊሶች፣ የስታድየም ጠባቂዎችና ጋዜጠኞች ብቻ ግን ይገኛሉ። በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ማተናገድ በለመደው በግዙፍ ስታድየም ውስጥ ሦስት መቶ ሰዎች ብቻ ተገኝተዋል።በሜዳው ጭንብል ከማድረግ ጀምሮ ተገቢው ጥንቃቄ ሁሉ እንዲደረግ ይጠበቃል። አሠልጣኞች ጮኸው መልእክት ማስተላለፍ ከፈለጉም 1.5 ሜትር ርቀት ላይ ሲሆኑ ብቻ አፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብላቸውን ማውለቅ ይችላሉ። ተቀያሪ ተጫዋቾች ደግሞ ተራርቀው ይቀመጣሉ። ከዛም በላይ አንድም ደጋፊ በስታድየሙ ውስጥ አይገኝም። በጥቅሉ እግር ኳስ ውበቱን በወረርሽኙ ተነጥቋል ማለት ይቻላል። ግን እንዳሉት ከሆነ ምንም ጨዋታ ካለማድረግ እንዲህ ባለ መልኩም ቢሆን መቀጠሉ ይሻላል። በዚህ የማይስማሙ ብዙ ቢሆኑም።አልጀዚራ ታድያ በዘገባው እንዲህ ሲል አስፍሯል፣ ‹‹ደጋፊ በሌለበት ባዶ ስታድየም ጎል ማግባት ይጨንቃል። ተጫዋቾችም ስሜታቸውን እንዲገቱ ነው የሚመከሩት››በኢንግሊዝ ፕሪምየር ሊግም ጨዋታዎች በዝግ ስታድየሞች በቅርቡ ይጀመራሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ቡድኖችም ወደ ልምምድ ገብተዋል። እንደውም ከሰሞኑ በወጣው መረጃ መሠረት የዋትፎርድ እና በርንሌይ ቡድኖች ውስጥ ቫይረሱ ያለባቸው ተጫዋቾች ተገኝተዋል።ቢቢሲ እንዳስነበበው ከሆነ አንድ ረዳት አሠልጣኝን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸው በምርመራ ተረጋግጧል። እነዚህ ሰዎች ራሳቸውን አግልለው ለቀናት እንዲቀመጡ ተመክረው በራቸውን ዘግተዋል። በድምሩም በሊጉ 748 ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ከ19 ክለቦች ምርመራ ተደርጎላቸዋል። እንዲያም ሆኖ ለቤተሰባቸው በመስጋት በቤት ውስጥ ልምምዶችን ማድረግን እንመርጣለን ያሉ ተጫዋቾች ጥቂት አይደሉም።ታድያ ይህ መሆኑ ምንአልባት በቅርቡ የሚለውን የሊጉን መጀመሪያ ጊዜ ሊገፋውና ራቅ ሊያደርገው ይችላል እየተባለ ነው።በኢትዮጵያስ?\nጥቂት የማይባሉ የአፍሪካ አገራት የውድድር ዓመቱን በመሰረዝ ስፖርት ጉዳይ አጀንዳ እንዳይሆን አድርገው ቋጭተውታል። በአፍሪካ ደረጃ የሚደረጉ የሻምፕዮን ውድድሮች የሁሉንም የአፍሪካ አገራት ውሳኔ የሚጠብቁ በመሆናቸው፣ እንደ ስምምነቱ አገራት ውሳኔያቸውን አሰምተዋል።ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊጉን ጨምሮ ሁሉንም ውድድሮች ሙሉ ለሙሉ መዝጋቷ የሚታወስ ነው። ይህም ብዙ ውዝግቦችን እያስነሳ ቢሆንም፣ እስከ ውሳኔው ጊዜ ድረስ ከዚህ የተሻለ አማራጭ አልተገኘም። በዚህም ታድያ ብዙ የእግር ኳስ ቡድኖች የሚከስሩ መሆናቸው ግልጽ ነው። በተለይም ከገንዘብ ጋር በተገናኘ የሚኖሩ ኪሳራዎች ቀላል የሚባሉ አይሆኑም።ከዛም ውጪ ውድድሩ ሙሉ ለሙሉ መቋረጡና የዓመቱ አሸናፊ እገሌ ነው አለመባሉ፣ የአፍሪካ ሻምፕዮና የሚካሄድ ከሆነ በሊጉ የነጥብ ሰንጠረዥ ቀዳሚ ላይ ያለው ቡድን ይሄዳል ወይስ ምን ይደረጋል የሚለውም አንዱ መነጋገሪያ ጉዳይ ነበር። በአንጻሩ የግብጽ ፕሪምየር ሊግ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ ሙሉ ለሙሉ የተሰረዘ ቢሆንም፣ የሊጉ ክለቦች በመስማማት በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ መሪነት ላይ የሚገኝ ቡድን በአፍሪካ መድረክ ይወክለናል በማለት ተስማምተዋል።የአገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ከቡድኖቹ ጋር ተወያይቶ አል አህሊና አል ሞካዉሎ የተባሉ ቡድኖች በአፍሪካ ሻምፕዮና፣ ፒራሚድና ዛማሌክ ደግሞ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ ይሳተፋሉ ብለዋል። ይሁን እንጂ የአፍሪካ ሻምፕዮናም ሆነ የኮንፌዴሬሽን ውድድሮች መካሄድ አለመካሄድቸው ላይ ገና የተባለ ነገር የለም።በኢትዮጵያም የእግር ኳስ ቡድን አመራሮች ተመሳሳይ ውይይት ማድረግ ይገባል የሚል አስተያየትን ሲሰጡ ይሰማል። አንዱ ውሳኔ ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮችን ስለሚያስነሳና ብዙ ውሳኔን የሚፈልግ ጉዳይም ስለሚከተል፣ ሰፋ ያለ ውይይት ማስፈለጉ ጥርጥር የለውም። ይህ በእንዲህ እንዳለ ታድያ የሚታየው መደጋገፍም ቀላል የሚባል አይደለም።በቅርቡ የወጣ ዘገባ እንደሚያስረዳው የቡና እግር ኳስ ክለብ አባላት ያልተከፈላቸውን የአንድ ወር ደሞዝ ቡድኑ እንዲይዘውና የኹለተኛውን ወር ደግሞ ግማሹን ብቻ እንዲከፍላቸው መስማማታቸው ይፋ ሆኗል። ከዛም አልፎ ቫይረሱን ለመከላከል በሚደረግ ጥረት የበኩላቸውን በማድረግም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ተስተውሏል።የፌዴሬሽኖች ፈተና\nየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ከስፖርት ኮሚሽን ጋር በመሆን 70ኛውን የፊፋን ስብሰባ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ነበር። ይህም አሁን ባለንበት ግንቦት ወር ይካሄዳል የተባለ ነው። በእርግጥ ይኸው ዓለም ዐቀፍ የእግር ኳስ ጉባኤ በቪዲዮ ሊካሄድ መወሰኑ ከሰሞኑ ተሰምቷል። ይህንንም ፌዴሬሽኑ በይፋዊ ድረ ገፁ ላይ አስፍሮታል።የእግር ኳስ ብቻ ሳይሆን ታድያ አትሌቴክስ ፌዴሬሽንም ቢሆን ለ2020 የቶክዮ ኦሎምፒክ በዝግጅት ዋዜማ ላይ ነበር። ይሁንና ኦሎምፒኩም ቢሆን ለ2021 ተራዝሟል። በ2021 ልሹ የሚካሄደው ቫይረሱ የጠፋ እንደሆነ እንጂ፣ በዚህ ከቀጠለ ውድድሮ ፈጽሞ ሊሰረዝ ይችላል የሚል ግምት ከወዲሁ እየተሰጠ ነው።\nባሕሩ ጥላሁን፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተጠባባቂ ዋና ሼል አስፈጻሚ እንዳሉት ከሆነ፣ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ብዙ ነገር ተቀይሯል። ወረርሽኙም የአመራሩን የዓመቱን እቅድ በሙሉ ነው ያዛባው ብለዋል። የሊግ ውድድሮች በጠቅላላ ታግደዋል። ‹‹ወደ መደበኛ የጊዜ ሰሌዳችን መቼ እንደምንመለስ አናውቅም። በጥቂት ሳምንታት ክረምቱም ይገባል። ሌላ መፍትሄ ካልተገኘ በቀር ሊጉን መጨረስ ከባድ ነው›› ሲሉም አስተያየት ሰጥተዋል።እንደ ፌዴሬሽኑ ከሆነ የዓመቱ አሸናፊ ማን እንደሆነ ሳይታወቅ፣ ከየዲቪዝዮኑ አላፊና ወዳቂው ሳይለይ ሊጉን ማቆም የመጀመሪያ አማራጭ መሆን የለበትም ነበር። ይሁንና ከዛ ውጪ አማራጭ የተገኘ አይመስልም።ክለቦች ታድያ ሁኔታው አልቀለላቸውም። ደሞዝ ለመክፈልም እየታገሉ ይገኛሉ። የክለብ ስፖንሰሮችም ቢሆኑ ከገበያ መቀዛቀዝ ጋር ተያይዞ ስምምነት ለመፈራረም ጊዜውን እያራዘሙ በመሆኑ ክለቦች ገንዘብ ማግኛ ምንጫቸው ሁሉ እየነጠፈ ነው። እንዲያም ሆኖ እንደምንም መክፈላቸውን ቀጥለዋል።በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ፌዴሬሽኑ ካለው ላይ ቀንሶ 500 ሺሕ ብር ቫይረሱን ለመከላከል ለሚደረገው እንቅስቃሴ ድጋፍ አድርጓል። ተጫዋቾችም በቤታቸው ውስጥ ሆነውም እንቅስቃሴ ከማድረግ እንዳይቆጠቡ እያሳሰበም ይገኛል።የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ስጋት ደግሞ ከዚህ ይለያል። ኦሎምፒክን ጨምሮ ሁሉም ዓይነት ውድድሮች በጊዜ ተሰርዘዋል። ከፍተኛ የአትሌቲክስ ሕክምና ባለሞያና የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን የጸረ ዶፒንግ ክፍል ተጠሪ ቅድስት ታደሰ እንደሚሉት፣ ይህ መሆኑ አትሌቶቹን እንዲሁም የአትሌቲክስ አገር የሆነችውን ኢትዮጵያን ይጎዳል። በእነዚህ ውድድሮች አለመሳተፋቸውም አትሌቶችን ብዙ እድል ያሳጣቸዋል። እንቅስቃሴያቸውን እንዲሁም ገቢያቸው ጭምር ይጎዳል።ውድድሮች ሰውነታቸውን እንዲጠብቁ ያግዛቸው ነበር የሚሉት ቅድስት፣ እንደ አገርም በዓለም ዐቀፍ መድረክ ልንታይ የምችልበትን እድል ነው ያጣነው ብለዋል። ከዛ የሚብሰው ደግሞ አትሌቶች ለቫይረሱ የበለጠ የመጠቃት እድል ያላቸው መሆኑ ነው።እንደ ዓለማቀፉ የስፖርት ሳይንስ ባለሞያዎች አስተያየት ከሆነ፣ አትሌቶች በውድድርና በከባድ ሥልጠና ውስጥ ከሆኑ ቫይረሱን የመከላከል አቅማቸው ይዳከማል። ቅድስትም በዚህ ላይ ሐሳባቸውን ሲጨምሩ ከመተንፈሻ አካል ጋር ለሚገናኝ በሽታ ተጋላጭ መሆናቸውን ነው ያነሱት። ‹‹አትሌቶቻችን በሩጫ ጽናታቸው ይታወቃሉ። ይህም የመተንፈስ አቅማቸውን እስከ ጥግ እንዲጠቀሙበት የሚያደርግ ነው። በዚህ ምክንያት ነው ቫይረሱ ምን ያህል ሊያጠቃቸው እንደሚችል መረዳት ያለባቸው›› ብለዋል።የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ታድያ ያለውን የአትሌቶች ትግል እንዲሁም ያለባቸውን ፈተና በመመልከት ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ የሥልጠና ቡድን አባላት፣ 4 ሚሊዮን ብር እና አስፈላጊ የተባሉ የሥልጠና ቅሳቁሶችን አሰራጭቷል። ‹‹ሁሉም 211 ብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድኖችና 56 አሠልጣኖች እያንዳንዳቸው 15 ሺሕ ብር ይከፈላሉ። ይህም ለማበረታቻና ባሉበት ጸንተው ራሳቸውንም እየጠበቁ እንዲቆዩ ነው ለማገዛ ነው።›› ብሏል፣ ፌዴሬሽኑ ባወጣው መግለጫ።ከአዲስ ማለዳ እህት መጽሔት ኢትዮጵያን ቢዝነስ ሪቪው በዐቢይ ወንድይፍራው የተጻፈውን መነሻ በማድረግ ፣ ወቅታዊ ተጨማሪ መረጃዎች ታክለውበት የተዘጋጀቅጽ 2 ቁጥር 81 ግንቦት 15 2012", "passage_id": "a502a9474a8e89c64e46e76599f85f27" }, { "passage": "እውን ቻይና ለባይደን ያላሰለሰ ድጋፍ እየሰጠች ነው? ትራምፕ አንገት ላይ ገመድ እያስገባች ነው?\n\nበመጪው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ሦስት አገሮች ስለአሜሪካ ከአሜሪካኖች በላይ ሊጨነቁ ይችላሉ። ቻይና፣ ሩሲያና ኢራን።\n\nእነዚህ አገሮች የሚፈልጉት ሰው እንዲመረጥ በይፋም በህቡዕም፣ በቀጥታም በእጅ አዙርም የሚችሉትን ሀሉ ከማድረግ አይቆጠቡም። ምክንያቱም በአሜሪካ ወደ ዋይት ሐውስ የሚዘልቀው ሰው ጎሮሯቸውን ሊከፍተው ወይም ሊዘጋው ስለሚችል ነው\n\nወራት ብቻ በቀሩት የአሜሪካ ምርጫ የትኛው አገር ማን እንዲመረጥ ይሻል? ለምን? የሚለውን በአጭሩ እንቃኝ። ለጊዜው ኢራንን እናቆያት።\n\nሩሲያ\n\nሩሲያ በባለፈው የ2016ቱ የአሜሪካ ምርጫ ዶልታለች፣ ፈትፍታለች የሚለው የአደባባይ ምስጢር ነው። ትራምፕና ወዳጆቻቸው ቢክዱትም። ፍርድ ቤት በቂ መረጃ አላገኘሁም ቢልም።\n\nየአሜሪካ ደኅንነት መሥሪያ ቤት እንደሚያምነው ሩሲያ ዶናልድ ትራምፕን የዛሬ 4 ዓመት ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት እጃቸውን ይዛ አስገብታቸዋለች። የትራምፕ ሰዎችና የሩስያ ሰዎች አብረው ሻይ ቡና ሳይሉ አይቀርም።\n\nየሳይበር ጥቃት በማድረግም ሒላሪን አሳጥተዋታል። ዲሞክራቶችን አሽመድምደዋል። የአገሬውን መራጭ ወደ ትራምፕ እንዲያጋድል በበይነ መረብ ጠልፈው ጥለውታል። አባብለውታል። ሩሲያ ይህን ለማድረግ በቂ አቅም ፈጥራለች።\n\nባለፈው ወር ሪፐብሊካኖች የመሩት የሴኔት ጉባኤ ሩሲያ ትራምፕ እንዲመረጡ ስለመፈለጓ ተጨማሪ መረጃን ሰጥቶ ነበር። ሆኖም ይህ ወንጀል ሆኖ ትራምፕን በሕግ የመጠየቁን ነገር አልገፋበትም።\n\nበ2020 ሒላሪ በባይደን ተተክተዋል። ሩሲያም ሒላሪን እንዳበሻቀጠች ባይደንን ነክሳ ይዛለች።\n\nየአሜሪካ የብሔራዊ ደኅንነትና ስለላ ክፍል ኃላፊ ዊሊያም ኢናቪና እንደሚሉት ምክትር ፕሬዝዳንት ባይደንን ለማደናቀፍ ሩሲያ ሁሉን አቀፍ ዘመቻ ከፍታለች።\n\nበሰሞኑ መደማመጥ በራቀውና የሰፈር ጎረቤታሞች ብሽሽቅ ይመስል በነበረው የቀጥታ የቴሌቪዥን ክርክር ባይደን ዶናልድ ትራምፕን \"የፑቲን አሻንጉሊት\" ሲሉ የገለጽዋቸው ወደው አይደለም። ትራምፕ ለፑቲን በይፋም በጓዳም አድናቆት አላቸው። ምናልባትም ከፖለቲከኛ እንደ ፑቲን የሚያስቀናቸው ሰው የለ ይሆናል።\n\nየኤፍቢአይ ዳይሬክተር ክሮስቶፎር ሬይ እንደሚያምኑት ሩሲያ መቼም ቢሆን በአሜሪካ ምርጫ ውስጥ መፈትፈቷን ትታ አታውቅም።\n\nከሁለት ዓመት በፊት በነበረው የሕዝብ ተወካዮች ምርጫ ሳይቀር ሩሲያ እጇን ማስገባቷን በመጥቀስ ክርስቶፎር ሬይ ክስተቱን \"ለ2020 ተውኔት ቃለ ተውኔት ልምምድ ላይ ያለች ትመስል ነበር\" ብለዋል።\n\nሩሲያ በበኩሏ እኔ በውጭ አገር ምርጫ ምን ጥልቅ አደረገኝ ስትል ድርጊቱን እንደካደች ነው። በዚህ የፈረንጆች ዓመት መጀመርያ የክሬምሊን ቃለ አቀባይ አሜሪካኖች የሚያቀርቡትን ክስ \"ደንብረው የሚዘላብዱት ነገር ነው\" ሲሉ ተሳልቀውበታል።\n\nሩሲያ ዶናልድ ትራምፕ ለ2ኛ ዙር ዋይት ሐውስ ቢቆዩላት ምርጫዋ ሲሆን ከዚህ በላይ የምትፈልገው ግን በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ትርምስን መፍጠር ነው ይላሉ የደኅንነት ጉዳይ አጥኚዎች።\n\nለምሳሌ የአውሮፓ ኅብረት አንድ ሰነድ እንደሚያስረዳው ከሆነ ሩሲያ ከአብዛኛዎቹ ኮሮናቫይረስን ከሚመለከቱ ሐሳዊ ዜናዎች ጀርባ ያለች አገር ናት። ይህን የምታደርገውም ትርምሱ ፖለቲካዊ ትርፍ ስለሚያስገኝላት ነው።\n\nጆ ባይደን ምን አሉ?\n\nባይደን ሩሲያን ጠንከር ባለ ቃል አስጠንቅቀዋል። ሩሲያ በሉአላዊት ልዕለ ኃያል አሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ እጇን አስገብታ መፈትፈቷን በቶሎ ካልገታች የምትከፍለው ዋጋ ይኖራል ብለዋል።\n\nየፑቲን አሻንጉሊት የሚሏቸው ዶናልድ ትራምፕም ከጠላት አገር ጋር መሞዳሞዳቸውን እንዲተዉ አሳስበዋል። \n\nባይደን በሩሲያ ላይ ያላቸው አቋም ይህን... ", "passage_id": "bff83a36ceadc9ccd0be5f8fd3edc150" }, { "passage": "የኮቪድ 19 ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ካመሳቀላቸው የሰው ልጅ ምድራዊ ስርዓቶች መካከል ቫይረሱ በማኅበራዊ ሕይወት የሚፈጥረውና የፈጠረው ማኅበራዊ ምስቅልቅሎሽ አንዱና ተጠቃሹ ነው። ይህም በአንድ ጀንበር የሚገለጥ ሳይሆን እያደር የሚታይ ሲሆን፣ ከምጣኔ ሀብት ድቀት ጋርም ዝምድናው የጠነከረ ነው። በተለይም የወረርሽኙን ስርጭት ለመከላከል የሚደረጉ ከቤት ያለመውጣትና የእንቅስቃሴ ገደብ መመሪያዎች የብዙዎችን ሕይወት እንዳልነበር አድርገዋል።አብርሐም ፀሐዬ ይህን ጉዳይ መነሻ በማድረግ በኡጋንዳ ካምፓላ የአንዲትን በወሲብ ንግድ የምትተዳደር ሴት ሕይወት በማሳያነት ያስቃኛሉ። እንዲህ ባለ ቀድሞም በተገለለ ሼል እንዲሁም ከፍተኛ ድህነት ውስጥ ያሉ ሰዎች ላይ ወረርሽኙ በተለየ የሚያደርሰውን ተጽእኖም ያስረዳሉ።በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ የወሲብ ንግዳችን በመቆሙ የረሃብ ስጋት ውስጥ ወድቀናል – ሞሬና (ካምፓላ – ኡጋንዳ)\nበ2018 በፊዚዮሎጂና በሜዲሲን ዘርፍ ከጄምስ ፒ. አሊሰን (James P. Allison) ጋር በጥምረት በመሆን የኖቤል ሽልማት አሸናፊ የሆኑት ጃፓናዊው ፕሮፌሰር ታሱኩ ሆንጆ (Tasuku Honjo) ስለኮሮና ቫይረስ የተናገሩት መረጃ የዓለምን ትኩረት ስቧል። ‹‹ይህ ኮሮና ቫይረስ ከሌሊት ወፍ መጣ የምትሉትን ቀልድ አቁሙ፤ በጭራሽ በባህሪው ተፈጥሯዊ አይደለም። ሆነ ተብሎ በቤተ ሙከራ የተፈበረከ ነው። ተፈጥሯዊ ቢሆን ኖሮ ቻይና ውስጥ እንደመከሰቱ የሚያስከትለው ጉዳትም እንደ ቻይና ተመሳሳይ የአየር ጸባይ ባላቸው አገራት ላይ ብቻ በተገደበ ነበር። ነገር ግን ከስዊዘርላንድ ጀምሮ እስከ በረሃማ አካባቢ ያሉ የዓለም ሕዝቦችን ሁሉ እያጠቃና እየገደለ የሚገሰግስ ሁሉን ገዳይ ቫይረስ ነው። ይህ ደግሞ የተፈጥሯዊ ቫይረስ ባህሪ ሊሆን አይችልም።›› ብለዋል።ሐሳባቸውን ሲያጠናክሩ ‹‹በእንስሳትና ቫይረስ ዘርፍ ከአርባ በላይ ዓመታትን በተመራማሪነት ሠርቻለሁ። በቻይና ዉሃን ግዛት ባለው የምርምር ጣቢያም ለአራት ዓመታት አገልግያለሁ። በዚያ ተቋም ያሉትን ባለሙያዎች ስለማውቃቸው የቫይረሱ ወረረሽኝ ከተከሰተ በኋላ በስልክ ለማግኘት ስደውልላቸው የሁሉም ስልክ ከአገልግሎት ውጪ ሆኗል። ይህ ግጥምጥሞሽ ሳይሆን ቴክኒሻኖቹ እንደሞቱ ያመላክታል” ብለዋል።ፕሮፌሰር ታሱኩ ‹ሰው ሠልሽ ቫይረስ ስለመሆኑ የተናገርኩት ውሸት ከሆነ ከምላሴ ጸጉር ይብቀል። በሕይወትም አልፌ ቢሆን እንኳን የሰጣችሁኝን የኖቤል ሽልማት አንሱት› ብለው ቫይረሱ የቻይና ሰው ሠልሽ ውጤት መሆኑን እንዲያምኗቸው አበክረው ተናግረዋል ።ኮሮና ቫይረስ የዓለምን መልክ ቀይሯል። ከቀድሞ በባሰ አለመተማመኑን አጉልቶታል። ፊታውራሪው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕም ኮሮና ቫይረስ ከማለት ይልቅ የ’ቻይና ቫይረስ’ እስከማለት ደርሰዋል። ከዓለም ጤና ጥበቃው አለቃ ከቴዎድሮስ አድኃኖም (ዶ/ር) ጋር የነበረው ውዝግብም በይፋ ሆነ ውስጥ ውስጡን አልበረደም። በተለይም ቴዎድሮስ ‹በጥቁርነቴ ‘ኔግሮ’ ተብዬ እስከመሰደብና የግድያ ዛቻ ሁሉ ተደርጎብኛል።› ብለው ይፋዊ መግለጫ ከሰጡ በኋላ፣ የጥቁሮችን እና የነጮችን ልሂቃን ለኹለት የከፈለ ሆኖ ታይቷል። ነገሩ ከጤና እና ሰብዓዊ ጉዳይነቱ ባሻገር የፖለቲካ አጀንዳ ማራገቢያ ወደመሆንም ተሸጋገሯል።ቤጂንግም ለጉዳዩ አጸፋዊ ምላሽ እየሰጠች በዛውም ቫይረሱን ስለመቆጣጠሯ እየገለጸች ብትገኝም፣ ኮሮና ቫይረስ ግን ያለማንም ከልካይ በየቀኑ የመግደያ ሰይፉን ወደአፎቱ ሳይመልስ አራት ወራትን አስቆጥሯል። ሚሊዮኖችን በማጥቃት ከኹለት መቶ ሺሕ በላይ ንጹሀንን ቀጥፎ አሁንም እየገሠገሠ ነው።\nኮቪድ 19 የበለጸጉ አገራትን የጤና ስርዓት ጉድለት አጋልጧል። ኃያሏ አሜሪካ እንደምጣኔ ሀብቱና ፖለቲካው በአዎንታዊ መልኩ ሳይሆን በተቃራኒው መንገድ ዜጎቿን በሞት መዝገብ በማስፈር ግንባር ቀደም ሆናለች። በአጠቃላይ ዓለም ልኳን አውቃለች። ገዳዩ ቫይረስ ሆን ተብሎ ተፈጥሯል ቢባልም ለዚህ ዓይነት ሰው ጨራሽ ክስተት ዓለማችን ለጊዜውም ቢሆን እጇን የሰጠች ይመስላል። የረቀቁ ቴክኖሎጂዎቿና የሳይንስ ምርምሮቿ አላስጣሏትም። በጎን ደሞ የክትባት/የመድኃኒት ግኝት ላይ ለመድረስ ፉክክሩ ተጧጡፏል።\nበኹለቱ የዓለም ጦርነቶች ማግስት እንደተከሰተው ሁሉ የምጣኔ ሀብት ቀውሱ ከበሽታው በላይ አስጊ እየሆነ ይመስላል። የዚህ የሦስተኛ የዓለም ጦርነት የሚመስለው ዝምተኛው የቫይረስ ቀውስ ትሪሊዮን ዶላሮችን አስወጥቷል ወይም አክስሯል። ከፍተኛ የነፍስ ዋጋ እየተከፈለበትም ነው። ምንም ያህል አስቸጋሪ ቢሆንም ሀብት ያላቸው አገራት ከተማቸውን ዘግተውና ሕዝባቸውን በቤት ሸሽገው የቫይረሱን ቀውስ ለማለፍ እየሞከሩ ነው።የአሜሪካ የነዳጅ ገበያ ከዜሮ በታች ወርዷል። ከሰማንያ በመቶ በላይ የዓለም አገራት የተባበሩት መንግሥታትን ገንዘብ ስጠን ብለውታል። የቱሪዝም ኢንዱስትሪዎች ቆመዋል፣ የሁሉም ዘርፍ ትራንስፖርት ተገትቷል። በአሜሪካ ወደ 26 ሚሊዮን ሕዝብ በአንድ ወር ተኩል ውስጥ ሼል ዕጥ ሆኗል። ወደሥራችን እንመለስ የሚሉ የግፊት ጥያቄዎች እየበረቱ ነው።የአገራችን የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ተቋም ጥናት እንዳመለከተው ደግሞ የዘንድሮ ዕድገታችን ከሦስት በመቶ እንደማይበልጥ ነግሮናል። ብዙ አገራት ዘግቶ የመቀመጥን ሕግ ተግብረው ለዜጎቻቸው ሕይወት ቅድሚያ ሰጥተዋል። የምጣኔ ሀብቱ ቀውስ ግን በጎን ሌላ በሽታ ሆኖ እየመጣ ነው።\nየአፍሪካን ምጣኔ ሀብት በአንዲት ሴት መነጽር እንመልከተው። ከሳምንታት በፊት ሮይተርስ ባስነበበው መረጃ በኡጋንዳ ካምፓላ በወሲብ ንግድ የተሰማራችን ሴት ሕይወት ከኮሮና ቫይረስ ስጋት ጋር አያይዞ ገልጾት ነበር። ጽሑፉ ‘Who is going to stand up for us?’ ‹ለእኛስ ማን ይደርስልናል?› በማለት በወሲብ ንግድ ውስጥ ያለችውን ሴት ንግግር በርዕስነት መርጦታል። አና ትዌት ሞሬና (Anna Xwexx Morena) ትባላለች።\nእንደሚታወቀው ካምፓላ ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ዜጎችንና ተቋማትን ከእንቅስቃሴ የሚገድብ ሕግ አውጥታ ነበር። ሞሬና ይህ ችግር ያስከተለባትን የሕይወት ምስቅልቅል ለጠየቃት ጋዜጠኛ ገልጻለታለች።‹‹ነገና ከዚያ ቀጥለው ባሉት ቀናት ሌላው ቀርቶ ምን እንደምበላ እንኳን እርግጠኛ አይደለሁም። መንግሥት ያወጣውን አዋጅ ተከትሎ፣ የወሲብ ደንበኞቻችን የነበሩት ከኛ ጋር መገናኘቱን እያቋረጡ መጥተዋል። ይህ ደግሞ ለኑሯችን ትልቅ ፈተና ሆኗል።›› ብላለች።መንግሥት የሰዎችን የእንቅስቃሴ ለሳምንት ያህል በዘጋበትና ገደብ በጣለበት ወቅት የተጠየቀችው ሞሬና፣ ይህ ሕግ ምናልባትም ለወር ከዘለቀ እንደሷ በተመሳሳይ ሼል ላይ የተሰማሩና የእርሷን ዓይነት ሕይወትና ኑሮ እየገፉ ያሉ ሰዎች ዕጣ ፈንታ በረሃብ መሞት እንደሆነ አስረድታለች። በተለይም የማኅበራዊ መገለል የደረሰባቸውና ራሳቸውን በተለያየ የኑሮ ጥላ ውስጥ ለደበቁ ሰዎች እንዲሁ በእለት ከእለት ገቢ የሚተዳደሩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ኮሮና ቫይረስ ሌላ ልሾ ምታት ሆኖባቸዋል።የካምፓላዋን ሴት ሁኔታ ወደአገራችን ብንመልሰው ኑሮን ለማሸነፍ ከቤተሰባቸውና ከሚያውቃቸው ሰው ርቀው በተለያየ የገቢ ምንጭ የተሰማሩ ወገኖቻችን አሉ። በየጊዜው አሃዙ እየጨመረ ያለው የልመና፣ የጎዳና እና የወሲብ ንግድ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ነዋሪዎችን ካየን፣ የምጣኔ ሀብትን እያሽመደመደ ከመጣው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር ተያይዞ ውጤቱ በልተው ማደር እስከማይችሉ ድረስ አደጋው በጣም አስቸጋሪ እንደሆነ መገመት ይቻላል።አንድ ሰበዝ መዘን ብናይ እንኳን ሆቴሎች ሥራቸው እየቀነሰ በመጣ ቁጥር ተረፈ ምግቡን የሚጠቀሙት የጎዳና ሕይወት ላይ ያሉ ወገኖቻችን የቀናትን ዕድሜ በማይሰጠው ረሃብ መጎዳታቸውን ለማሰብ ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው። መደበኛው የምጣኔ ሀብት ቀመራችን እምብዛም ትኩረት የማይሰጠው የተሳሰረ አኗኗራችን ብዙዎችን በስሩ ያቀፈ ነው። ከቫይረሱ የሞት ስጋት ይልቅ የረሃብ ስጋቱ ሊገዝፍ ይችላል። ይህንኑ ስጋት ተከትሎ የሚመጣው ምስቅልቅል ከባድ ስለመሆኑ ባለሙያዎች ከአሁኑ ግምታቸውን እያስቀመጡ ነው።በኹለት አሃዝ አደገ ተብሎም የእያንዳንዱን ጓዳ መሙላት ያልቻለው ምጣኔ ሀብታችን እስከ 2.3 እንደሚወርድ ተነግሯል። እዚህ ላይ ከወዲሁ ትልቅ የቤት ሼል እንዳለና እንደሚጠይቅ ማመላከቻ ነው። ችግራችን የዋዛ አይደለም። ይህንኑ ማስረገጫ የሚነግረን የረሃብ ስጋት ካለባቸው ጥቂት የዓለም ሀገራት ተርታ መቀመጣችን ነው።\nወደ ጀመርነው የኡጋንዳዋ ካምፓላ ስንመለስ በወሲብ ንግድ ውስጥ ያለችው የሞሬና ስጋት ጥሩ ማሳያ ይሆናል። ዕድገቷን ጨረፍ አድርገን እንለፍ። ገና ስትወለድ ወንድ እንደነበረችና በሂደት ግን እንግዳ የሆነ የጾታ፣ ሥነ ባህሪና የስርዓተ – ጾታ ምስቅልቅል በራሷ ላይ ተመለከተች። እናቷን በሕጻንነቷ አጥታ ከእንጀራ እናቷና ወላጅ አባቷ ጋር ለመኖር የተገደደችው ሞሬና ለጓደኞቿ ሁኔታውን ብትነግራቸውም እንኳን ሊረዷት እንዳልቻሉ ትናገራለች።\nበመጨረሻም በተለያዩ የጾታዊ፣ የስርዓተ ጾታ ጉዳዮች ላይ የሚሠራ ተቋም ጋር በመሄድ ያለባትን የጾታ መፋለስ ለማወቅ ችላለች። ቤተሰቦቿ ግን ይህንን ከሰሙበት ዕለት ጀምሮ በማግለላቸው የተነሳ እሷም ሴትነቷን መርጣ በመሰል ሕይወት ውስጥ ካሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር የወሲብ ንግዱ ጎራ ውስጥ ተቀላቅላለች።ይህ ሕይወቷ በኮሮና ቫይረስም ሰለባ ከመሆን አልዳነም። ስለካምፓላ የእንቅስቃሴ ገደብና የገቢ ምንጯ መድረቅ ስታብራራ ‹‹የሕክምና ማእከላት ሥራቸው በመስተጓጎሉ በሆስፒታል ውስጥ የማገኘውን የኤች አይቪ ኤድስ ክትትል እንኳን ማግኘት አልቻልኩም፤ ገቢዬ ቆሟል። ሼል ባለኝ ጊዜ በወር እስከ 160 ሺሕ ሽልንግ (42 ዶላር) አገኝ ነበር። ከዚህ ላይ 130 ሺሕ ለቤት ኪራይ፣ የተረፈውን ደሞ ለሌሎች ወጪዎች አብቃቃ ነበር። ይህ የእንቅስቃሴ ገደብ ሕግ ለአንድ ወር እየገፋ ከሄደ የመኖር ህልውናዬ አደጋ ውስጥ ነው›› ስትል ገልጻለች።\nከኮሮና ጋር ተያይዞ የኑሮ ውድነቱን የተናገረችው ሞሬና ካምፓላ ላይ ያለውን የሸቀጥ ዋጋ ስትገልጽ ከዚህ በፊት አንድ ኪሎ ስኳርን በ4500 ሽልንግ ትገዛ እንደነበርና አሁን ላይ ግን የሃምሳ በመቶ ጭማሪ አሳይቶ 6500 ሽልንግ ስለመድረሱ ተናግራለች። ‹‹በጥቅሉ በፈጣሪ ዕርዳታ እስከ አሁኗ ቀን ያለችውን ኑሮዬን እየገፋሁ ነው። ነገ ላይ ግን እንጃ…›› በማለት የመነመነ ተስፋዋን ለጋዜጠኛው አጋርታዋለች።ተጨማሪ ስጋቷን ስትገልጽም ‹‹እኛ እንድንወጣ ቢፈቀድልን እንኳን የተገለልን የማኅበረሰብ ክፍል ከመሆናችን ጋር ተያይዞ ሊያጠቁን የሚችሉ ቡድኖች ይኖራሉ።›› ብላለች። መንግሥት ደግሞ ወረርሽኙ ላይ እንጂ ተያያዥ ጉዳዮችን ትኩረት ሊሰጥ አይችልም የሚል ፍራቻ አላት። የተለያዩ ምሁራን በአንድም ይሁን በሌላ ከዚህ ጋር ተመሣሣይነት ያላቸው የማኅበረሰብ ቀውሶች ይፈጠራሉ ባይ ናቸው። እንደዝርፊያና ከፍ ያሉ የውንብድና ችግሮች የምጣኔ ሀብት ቀውሱ የሚወልዳቸው ስጋቶች እንደሚሆኑም ከወዲሁ እየተተነበየ ነው።\nሞሬና ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደኛ ያሉ በወሲብ ንግድ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በቂ የሆነ የሥነ ልቦና እና የኑሮ ድጎማ እስካልተደረገላቸው ድረስ ራስን እስከማጥፋት የሚደርስ ውሳኔ ላይ እንደሚገቡ ግምቷን አስቀምጣለች።ይህ አንዲት ተነጣይ ታሪክ እንደሚነግረን በአገራችንም ይሁን እንደኛ ባሉ ደሃ አገራት ውስጥ ሌሎች ሳይነገሩ ራሳቸውን በየቀዳዳው የደበቁ ነገር ግን ጊዜያቸውን እየጠበቁ ተከታትለው የሚፈነዱ የማኅበራዊ፣ የምጣኔ ሀብትና ፖለቲካዊ ቦንቦች አይኖሩም ማለት ሞኝነት ነው። የኮሮና ሻይረስ ምስቅልቅል በብልሃት የሚያዝ እንጂ እንዲሁ በደመነፍስ የሚፈታ ችግር ባለመሆኑ ትልቅ የመውጫ ቀመር ከልሂቃኑ የሚጠበቅ ይሆናል። ቸር ያሰማን!!!አብርሐም ፀሐዬ የቢዝነስ አማካሪና ጋዜጠኛ ሲሆኑ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ላይ ይገኛሉ።ቅጽ 2 ቁጥር 78 ሚያዝያ 24 2012", "passage_id": "9fcfed7b207df3980477ebf7352a3201" } ]
f68ce4769a660a6e00ef047d60af66d3
7d1c97ca5be7fde3506bae56ae7df06b
የስፖርት አጋርነት በኮሮና ቫይረስ ውጊያ
  በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። የወቅቱ የዓለም ራስ ምታት በሆነው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር በተያያዘም ስፖርት መገኘት ባለበት ሁሉ አጋርነቱን በማስመስከር ላይ ይገኛል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮችን ከማቋረጥና ከመሰረዝ ባለፈ የስፖርቱ ተዋንያን በተናጥልም ሆነ በተቋማዊ ደረጃ አበርክቷቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በእግር ኳስ ጠቢብነታቸው ዓለም የመሰከረላቸው ተጫዋቾችና ስመ ጥር አሰልጣኞችም፤ ለደጋፊዎቻቸው መልእክት ከማስተላለፍና ገንዘብ ከመለገስ ባሻገር ሆቴሎቻቸውን ለህክምና አገልግሎት እንዲውሉም ጭምር መስጠታቸው ይታወሳል። ክለቦችም በተመሳሳይ ስታዲየሞቻቸውን ቫይረሱን ለመዋጋት ለሚደረገው ጥረት እያዋሉት ይገኛሉ። የነጫጮቹ ስታዲየም ሳንቲያጎ በርናባው ለቫይረሱ የሚሆኑ መድሃኒቶችና የህክምና እቃዎች ማከማቻ በመሆን እያገለገለ ይገኛል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ተከትሎ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እየደረሰ እንደሚገኝ ይታወቃል። ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያንቀሳቅሱ ዘርፎች መካከል አንዱ የሆነው ስፖርትም በዚሁ ምክንያት የገንዘብ ችግር በማስተናገድ ላይ ይገኛል። ከዚህ ጋር በተያያዘም የፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች ለተጫዋቾቻቸው ሙሉ ደሞዛቸውን መክፈል ከማይችሉበት ደረጃ ደርሰዋል። ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በጊዜያዊነት እስከ መጪው ወር መጨረሻ ድረስ መቋረጡ ይታወሳል። ክለቦች ከስታዲየም ገቢ እና ለሌሎችም የሚያገኙት ገቢ ላይ መቀነስ ተከትሎ ከፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ተጫዋቾቹ የደመወዛቸው ግማሽ እንዲከፈላቸው በመስማማት ስፖርት የመተሳሰብ መድረክ መሆኑን አረጋግጠዋል። ጥያቄውን በቅድሚያ ያቀረበው የሊጉ ክለብ የሆነው በርሚንግሃም ሲቲ ሲሆን፤ ለአራት ወራት በዚህ መልክ ደመወዝ እንደሚከፍል ማስታወቁን ዘጋርዲያን በዘገባው አስነብቧል። ቅድሚያ አንዳንድ ተጫዋቾች ሃሳቡን ባይቀበሉም በሂደት በበጎ ፈቃደኝነት መስማማታቸውን አሳይተዋል። ክፍያው ከተጫዋቾችና የአሰልጣኞች ቡድን ባለፈ ያሉ የክለብ ሰራቶችን እንደማይመለከትም ታውቋል። ወደ ኢትዮጵያ መለስ ስንልም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 2 ሚሊዮን ብር ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል እንዲሁም ለታላቁ የህዳሴ ግድብ መስጠቱ ከትናንት በስቲያ የተሰማ ዜና ነው። ይህም ብቻ ሳይሆን የፌዴሬሽኑ ተቀዳሚ ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉም በግሏ ለጤና ሚኒስቴር እንዲሁም ለታላቁ የህዳሴ ግድብ በድምሩ 400ሺ ብር መለገሷ ታውቋል። የኢትዮጵያ ዳኞችና ታዛቢዎች ሙያ ማህበርም በበኩሉ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የ 50ሺ ብር ድጋፍ አድርገዋል። የወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ምክትል ፕሬዚዳንት የገንዘብ እንዲሁም የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ለመጓጓዣ እንዲውል የተሽከርካሪ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ሶከር ኢትዮጵያ በድረ ገጹ አስነብቧል። ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29350
[ { "passage": "ኃያላኑን አገሮች ጨምሮ የዓለም ሳይንቲስቶች ከሁሉም በፊት ትኩረታቸውን በአንድ ነገር ካደረጉ አራት ወራት አለፈ።በቻይና ውኃን ግዛት በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት መባቻ ለተከሰተውና በምህፃረ ቃሉ ኮቪዲ 19 የሚል መጠሪያ ላገኘው ኮሮና ቫይረስ።ወረርሽኙ ዘር፣ ቀለም፣ ትንሽና ትልቅ ሳይለይ ሁሉንም በማጥቃት የአለም ህዝብ በፍርሃት አቁማዳ ውስጥ እንዲገባ ካደረገ አራት ወራቶች አልፈዋል። በእነዚህ ወራት የወረርሽኙን ስርጭት ለመግታት የቻለ ምድራዊ ኃይል አልተገኘም። የአለም ሀያላን አገራት ከምድር ተሻግረን ጨረቃ ላይ እንወጣለን ሲሉ እንዳልተመፃደቁ፤ የኮሮና ወረርሽኝ ከቤታቸው ራሱ እንዳይወጡ አደረጋቸው። \nሀገራቱ የወረርሽኙን ስርጭት በቶሎ የመቆጣጠር አቅም በማጣታቸው በአራት ወራት ብቻ ከሁለት መቶ ሺህ ሰዎች በላይ ህይወት ተቀጠፈ። የአለም ህዝብን እንደ ቅጠል ከማርገፍ በተጨማሪ በተለያዩ የንግድ ተቋማት ላይ ይህ ቀረሽ የማይባል ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውስ አስከትሏል። የኮቪድ 19 ስርጭት በማይታመን ፍጥነት ከመጨመር በተጓዳኝ መድሃኒት አልባ በመሆኑ ሀገራት ትኩረታቸውን ሁሉ ቅድመ መከላከል ላይ መስራትን መርጠዋል። ኢትዮጵያም የአለም ሀገራትን በአንድ ልብ እያስጨነቀ ካለውን ጠላት ህዝቦቿን ለመታደግ በብሄራዊ ደረጃ መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችሉ ሥርዓቶችን በመዘርጋት እየተንቀሳቀሰች ትገኛለች። መንግስት የወረርሽኙ ባህሪ ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ አቋም አኳያ ስርጭቱ ከፍተኛ ሊሆን እንደሚቸል በመገንዘብ ለህዝቡ ጥሪ በማድረግ የጋራ ተሳትፎን ያማከለ እንቅስቃሴ ሲደረግ ቆይቷል። በዚህ ተግባር ላይ የተለያዩ አካላት ተሳትፏቸውን ባሳዩበት ተግባር ላይ በስፖርቱ ዘርፍ ባሉ አካላት በኩል አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት የነበራቸው ተሳትፎ ትልቅ እንደነበር ለመታዘብ ተችሏል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ከታወቀበት ከመጋቢት መጀመሪያ ሳምንት ጀምሮ በቡድንም ሆነ በተናጠል ለወረርሽኙ መከላከያ የሚውል የገንዘብ ድጋፍ በማሰባሰብ ነበር ይሄንኑ ያስመሰከሩት። \nየስፖርቱን ተቋማት ከሚመሩት አካላት ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከወራት በፊት መንግስት ላቀረበው ጥሪ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ያሳዩት ተሳትፎ ዳግም\n ማሳየተቻው ተነግሯል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን በጋራ ለማሸነፍ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ ከሳምንታት በፊት የማዕድ ማጋራት ብሔራዊ ጥሪን አድርገው ነበር። የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ከቢ. ጂ አይ ኢትዮጵያ በጋራ በመሆን በሳምንቱ መጨረሻ ላይ አንድ መርሃ ግብር ይፋ አድርገዋል። የስፖርቱ ተቋማት በኩል ይፋ የተደረገው መርሃ ግብር ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ ማጋራት ብሄራዊ ጥሪ»ን እውን ያደርጋል ተብሏል። መጋቢት መጨረሻ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ “ማዕድ ማጋራት” ሲሉ በሰየሙት መንገድ መንግስት የኮሮና ወረርሽኝ የከፋ ጉዳት ቢያደርስ በየቤቱ ምግብ ለማድረስ አቅሙም ሆነ መንገዱ ስለማይኖረው፤ ሰዎች በምግብ እጦት እንዳይጎዱ አንድ ቤተሰብ በቀን አንድ ምግብ ሌላ ቤተሰብ ለማቅረብ ዝግጅት እንዲደረግ እና እንደቤተሰብ ምክክር እንዲደረግ ሲሉ ነበር ያሳሰቡት። የጠቅላይ ሚኒስቴሩን ጥሪ ተከትሎ በርካቶቸ ምላሽ ሰጥተዋል። የስፖርት ተቋማቱ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት ሰሞኑን ይፋ ያደረጉት የምገባ መርሃ ግብር ይሄንኑ መሰረት አድርጓል። በዚህ መርሃ ግብር 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል እንደሚመግብ ተነግሯል። \nየስፖርቱ ን ማኅበረሰብ ህዝባዊነት የሚያረጋግጥ መሆኑ የተነገረለት መርሃ ግበር ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲጀመር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እንደተናገሩት፤ የኮሮና ቫይረስ ወደ ሀገራችን ከገባ ጀምሮ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የስፖርቱ መንግስታዊ እና ህዝባዊ አደረጃጀቶች፣ ታዋቂ አትሌቶች፣ የደጋፊ ማህበራት፣ በአጠቃላይ የስፖርት ቤተሰቡ ህብረተሰቡን በማንቃት እና ኢኮኖሚያዊ ጫናውን ለመቋቋም የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን መወጣታቸውን አስታውሰዋል። የስፖርቱ ማኅበረሰብ ድጋፍ ተጠናክሮ የሚቀጥልና የምገባ መርሃ ግብሩ መጀመር ለዚሁ ማሳያ ይሆናል ብለዋል። \nየጎዳና ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን በተወሰነ መልኩ ለማገዝ አንድ ወር የሚቆይ የምገባ መርሃ ግብሩ ይሄንኑ ሚና መሰረት ባደረገ መልኩ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ኤልያስ፤ በስታዲየም ዙሪያ መርሃ ግብሩ እንዲደረግ የተመረጠበትን ምክንያት መኖሩን አመልክተዋል።« በወቅታዊ የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ስርጭቱን ለመቆጣጠር ሲባል በተለይ ስታዲየም ዙሪያ የሚገኙ ባር እና ሬስቶራንቶች መዘጋታቸው እና በአካባቢው ያለው እንቅስቃሴ መቆሙ ይታወቃል። ሬስቶራንቶች መዘጋታቸውን ተከትሎ ከሬስቶራንቶች ተመላሽ የሚሆኑ ምግቦችን ይጠቀሙ የነበሩ የጎዳና ተዳዳሪዎችም ሆነ በስታዲየም አካባቢ የተለያዩ ነገሮችን በመሸጥ ይተዳደሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል። በመሆኑም ጊዜው የከፋ ችግር ላጋጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እጃችን የምንዘረጋበት፤ የጋራ መከራችንን በመተጋገዝ የምናልፍበት መሆኑን በማመን እና ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ነው »ሲሉ አብራርተዋል። አቶ ኤልያስ በመጨረሻ የተጀመረው ተግባር የሚቋረጡ ሳይሆን በቀጣይም እነዚህ ወገኖቻችን በዘላቂነት ህይወታቸውን ሊመሩበት በሚችሉ ጉዳዮች ላይ የስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ አቅሙ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የቢጂ አይ ኢትዮጵያ አመራሮች በጋራ በመሆን ባስተላለፉት መልዕክት ደግሞ፤ የምገባ መርሃ ግብሩ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። \n«በአሁኑ ሰዓት የገጠመንን ፈተና ለማሸነፍ ለመንግስት ብቻ የሚተው ባለመሆኑ ሁሉም በአቅሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል »ያሉት ደግሞ፤ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ናቸው። ሚኒስትሯ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የምገባ ፕሮግራም ለሌሎች ድርጅቶች እና ባለሀብቶች አርዓያነት ያለው ተግባር መሆኑም ገልጸዋል። በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ያቀረቡትን የማዕድ ማጋራት ብሔራዊ ጥሪ ተከትሎ የስፖርት ቤተሰቡ እና አመራሩ በዚህ በጎ ተግባር መሳተፉ ሊያስመሰግነው እንደሚገባ አመልክተዋል። \nየኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ከቢ. ጂ አይ ኢትዮጵያ በጋራ በመሆን ሚያዚያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ይፋ ያደረጉት መርሃ ግብር ለአንድ ወር ያህል የሚዘልቅ ይሆናል። በመርሃ ግብሩ 300 ሰዎች ተጠቃሚ የሚሆኒ ሲሆን ተመጋቢዎቹ በቀን 2 ጊዜ እንዲመገቡ ይደረጋል። የተጠቃሚዎች ዝርዝር በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 7 የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት አማካኝነት ተለይተው እንዲቀርቡ የተደረጉ ናቸው። ለምገባ ፕሮግራሙ ከ800 ሺ ብር በላይ ወጪ የሚደረግ መሆኑ ታውቋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 20/2012\nዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "9244288241948d956f1e17db20f07627" }, { "passage": " ከዓለም እስከ አህጉር፣ ከአህጉር እስከ አገር፣ ከአገር እስከ መንደር ከዚያም ማህበረሰብ እስከ ግለሰብ፣ በስፖርት ልቡ ያልተሳበና በፍቅሩ ያልተንበረከከ የለም።ስፖርት ሰላም ፣ፍቅር ፣የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም።ሁለት የተለያዩ አገራት ያወዳጃል። በአገር ፍቅር ስሜት ያስተሳስራል።ያፋቅራል።በእርግጥ አንዳንዶች ውጤትን ከስፖርታዊ ጨዋነት አስበልጠው የግል ጥቅማቸውን ሲያስቀድሙ ይስተዋላል። ከዚህ በአንፃሩ የግል ፍላጎታቸውን ችላ በማለት በስፖርታዊ ስነ ምግባር የታነፁ መኖራቸው የማይካድ ሃቅ ነው።በአትሌቲክሱ የውድድር ፍልሚያ ኬንያውያን በተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ውድድሮች ላይ በርካታ ወገኖችን አስደንቀዋል።አስጭብጭበዋል።በውድድር አሸናፊ ሆነው የታዩትን ያህልም ከአንዴም ሁለት ጊዜ በስፖርታዊ ጨዋነትና ሰብዓዊነት ተግባር የታነፁ ስለመሆናቸውም አስመስክረው የሚሊየኖችን ልብ ሲያሸንፉ ታይተዋል።።የምስራቅ አፍሪካዊቷ አገር አትሌት ከሰሞኑም ይህን በስፖርታዊ ጨዋነት መርህ የታነፀ ሰብዓዊነት ተግባር ደግሞ አሳይቷል።ትዕይንቱ የተከሰተው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማህበር የነሃስ ሜዳሊያ በሚሰጠውና ከቀናት በፊት በተካሄደው የናይይጄሪያ ዓለም አቀፍ የ10 ኪሎ\nሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ነው።የታሪኩ ባለቤት ሲሞን ቺፕሮት ይባላል።ኬንያዊ የረጅም ሩጫ አትሌት ነው።በዚህ የ10 ኪሎ\nሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ሲሳተፍ አራተኛው ሲሆን፣ ከሶስት ዓመት በፊት ደግሞ ባለድል መሆን ችሏል።ባሳለፍነው አመት ደግሞ ሁለተኛ ሆኖ ጨርሷል።ክስተቱ እንዲህ ነው። ሲሞን ቼፐሮት የዘንድሮውን ውድድር እየመራ ለመጨረስ የተወሰኑ ሜትሮች ብቻ ቀርተውታል።ውድድሩን ለሁለተኛ ጊዜ በማሸነፍ የመጀመሪያው የሚሆንበትን ታሪክ ለመፃፍ ማንም ሊያቆመው አይቻለውም።ይሁንና በዚህ ቅፅበት ሌላኛው የአገሩ ልጅና ብርቱ ተቀናቃኙ የሆነው ኬኔት ኪፕኬሞይ ድንገት ሲዝለፈለፍ ይመለከታል።ክስተቱን ያስተዋለው ሲሞን ቼፕሮት ግን የአገሩን ልጅ ጥሎት ለመግባት አልወሰነም።ውድድሩን አሸንፎ አንደኛ የመባል ስሜቱን አላዳመጠም።ውድድሩን ለሁለተኛ ጊዜ በማሸነፍ የመጀመሪያው የሚሆንበት ታሪክ ለመጻፍ አልቸኮለም።አትሌቱ የተፎካካሪውን ውድቀት እንደ መልካም አጋጣሚ ከመጠቀም ይልቅ ብዙዎቹን ባስገረመ መልኩ ሩጫውን በማቋረጥ ጓደኛውን ከወደቀበት ደግፎ አንስቶ ልባዊ ወንድምነቱን በማሳየት በርካታ ወገኖችን አስደምሟል። ሁለቱ አትሌቶችም ቀስ ብለው በመሮጥ ውድድሩን 15ኛ እና\n16ኛ ሆነው የፈፀሙ ሲሆን አንደኛ መውጣት የሚችለው ሲሞንም ተሸንፏል።አትሌቱ ከፊቱ የሚጠብቀውን የወርቅ ሜዳሊያና የአሸናፊነቱን ሽልማት ገንዘቡን በመተውና ይህ ሁሉ ከሰው እንደሚያንስ በማሳብ የፈፀመው መልካም ተግባር በሚሊየን የሚቆጠሩ ልቦችን ማሸናፍ ችሏል።የወርቅ ሜዳሊያውን ትቶ ከወርቅ በላይ የሆነ ጀብዱ በመፈፀም፤ ከወርቅ ሜዳሊያው ይልቅ ሰብአዊነት እንደሚልቅ ለመላው ለዓለም   አሳይቷል።ሜዳሊያ ሳይሆን ልብ ያሸነፈውና በውድድሩ ስፍራ ሆነው ውድድሩን የተመለከቱትን በሺዎች የሚቆጠሩ ብቻም ሳይሆን በአህጉር ዓቀፍ ደረጃ በቴሌቪዥን መስኮት የሚመለከቱትን ያስደነቀ አትሌት ፤ማሸነፍ ማለት ሁሌ አንደኛ መውጣት ማለት አይደለም፤ሁሌ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኛት አይደለም። አንዳንዴ ተሸንፈህ አሸናፊ ትሆናለህ፣ መጨረሻ ወጥተህ ክብርን ጀግንነትን ትጎናፀፋለህ አሰኝቷል።‹‹በአንድ ወቅት አባቴ፤ በመንገድህ ላይ የታመመ ሰው ስትመለከት አልፈኸው ጉዞህን አትቀጥል፤ ይልቅ እርዳው፤ ብሎኝ ነበር፤ የአገሬውን ልጅ ወድቆ ስመለከተው ይህ ወደ አእምሮዬ መጣ፤ እናም ለራሴ ሳላስብ ልረዳው ወሰንኩ ››ያለው አትሌቱ፤ መሰል ተግባሩም ለመጪው ትውልድ አርእያነት ያለው ስለመሆኑ ተናግሯል።የአትሌቱ ተግባርም የወርቅ ሜዳሊያ ከማግኘት ይልቅ ወርቃማ ልብ መያዝ ይበልጥ ያነግሳልና ይህም እውነተኛው የስፖርት ጽንሰ ሃሳብ መገለጫ ነው አሰኝቷል። በዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር የናይጄሪያ ተወካይ ማይክ ልቴሟግቦር አትሌቱን ‹፣ጀግናችን››ሲሉ አሞካሽተውታል፡፡ለፈፀመው የሰብዓዊነት አኩሪ ገድልም አንድ ሚሊየን ሽልንግ አበርክተውለታል።የቺፕሮትን ተግባር\nበማወደስ፤ ተረጂው አትሌት\nበበኩሉ፤ ‹‹ሁሉም አትሌት\nይህን መሰል ተግባር\nአይፈፅምም፤ሲሞን መልካም\nሰው ነው፤ በውድድሩ\nእኔን ለማርዳት ያሰው\nመልካምነትም እጅጉን አስድንቆኛል››\nሲል ተደምጧል። አሸንፎ\nሜዳሊያውን ከወሰደው ኢትዮጵያዊ\nበላይ ሲሞን ጀግና\nተብሎ ዘላለማዊ ስምና\nዝናን አትርፏል።አዲስ ዘመን ግንቦት 27/2011 ", "passage_id": "ea9ee4c32daedd909149824d13b5ab5d" }, { "passage": "በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር በሚኖር ቅርብ ግንኙነት እና ንክኪ እንዲሁም ታማሚው በሚስልበት ወቅት በአየር ላይ በሚለቀቁ ጠብታዎች (droplets) አማካኝነት የሚተላለፈውን ቫይረስ ስርጭት ለመቆጣጠር የተለያዩ ጥረቶች ቢደረጉም ወደተለያዩ ሃገራት እንዳይዛመት ለመከላከል አልተቻለም። በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥም ኢትዮጵያን ጨምሮ 133 ሃገራትን ሲያዳርስ ከ138,000 በላይ ሰዎችን አጥቅቶ ለ5000 ሰዎች ህይወት ማለፍ ምክንያት ሆኗል። የዓለም የጤና ድርጅት በመጀመሪያ በዓለምአቀፍ የጤና ስጋት ደረጃ ያስቀመጠው በሽታም ወደ ዓለምአቀፍ ወረርሺኝነት (Pandemic) ተቀይሯል።ከዓለማችን ህዝብ ከግማሹ በላይ የሚከታተለው እግርኳስም እንደማንኛውም የህይወት ክፍል የዚህ ወረርሺኝ ተፅዕኖ እንዲያርፍበት ሆኗል። በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች በየስታዲየሙ እየተገኙ የሚከታተሏቸው ጨዋታዎችም ለቫይረሱ ስርጭት የተመቸ ሁኔታን ሊፈጥሩ የሚችሉ እንደመሆናቸው የየሃገራቱ የጤና ጥበቃ ተቋማትና ውሳኔ ሰጪ ሰዎችን ትኩረት መሳባቸው አልቀረም። ወረርሺኙ ከተነሳባት ቻይና ጀምሮ የተለያዩ ሃገራት ክለቦች፣ ሊጎች፣ የእግርኳስ ማህበሮች፣ ብሎም እስከ ዓለምአቀፉ የእግርኳስ ማህበር ፊፋ ድረስ ከጤና ተቋማቱ ጋር በመተባበር ስርጭቱን ለመከላከል እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ።የቫይረሱ መነሻ የሆነችው ቻይና በየካቲት ወር ጀምሮ ታህሳስ ላይ የሚጠናቀቀውን የቻይና ሱፐርሊግ የሚጀመርበትን ቀን ላልተወሰነ ጊዜ አራዝማለች። ሃገሪቱ የቫይረሱን ስርጭትና የአዳዲስ ተጠቂዎችን ቁጥር በተወሰነ መልኩ ለመቆጣጠር ብትችልም ውድድሩ ግን እስካሁን ድረስ አልተጀመረም። ከእግርኳስ ሊጉ በተጨማሪም በቻይና ሊደረጉ የታሰቡ የእስያ ቻምፒዮንስ ሊግ፣ የሴቶች እግርኳስ የኦሎምፒክ ማጣሪያ፣ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና፣ የፒጂኤ የጎልፍ ውድድር፣ የፌድካፕ የቴኒስ ውድድር፣ የቻይና ግራንድ ፕሪ የሞተርስፖርት ውድድር እና የተለያዩ የቶክዮ ኦሎምፒክ የማጣርያ ውድድሮችን ጨምሮ በርካታ ስፖርታዊ ኩነቶች ተሰርዘዋል፣ ተሸጋግረዋል፣ ወይንም ወደ ሌላ አዘጋጅ ሃገር ተቀይረዋል። ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታም ባለፉት ሶስት ወራት ህዝብ የሚሰበሰብባቸው ስፖርታዊ ውድድሮች በቻይና እንዳይከናወኑ ተደርጓል።የእግርኳስ ደረጃቸው ከፍተኛ የሆኑ ሃገራት በሚገኙባት አውሮፓም የእግርኳሱ ባለድርሻ አካላት የቫይረሱን ስርጭት በመከላከል እና የእግርኳስ ካሌንደሩን ለመጠበቅ፣ ውድድሮች የሚያመነጩት ገቢም እንዳይነጥፍ በማድረግ ተፃራሪ ምርጫዎች ውስጥ የተለያዩ ውሳኔዎችን ሲያሳልፉ ቆይተዋል። የአውሮፓ እግርኳስ ማህበርም የቻምፒዮንስ ሊግ እና ዩሮፓ ሊግ ውድድሮች የሚጠናቀቁበትን ሂደት እና የ2020 የአውሮፓ ዋንጫ ዕጣፈንታን ለመወሰን አባል ሃገራቱን በመሰብሰብ በመወያየት ላይ ይገኛል። የአውሮፓ ዋንጫን ከማራዘም፣ የውድድሩን አዘገጃጀት እና ቅርፅ መቀየር፣ አልፎም የቻምፒዮንስ እና ዩሮፓ ሊግ ውድድሮችን እስከመሠረዝ ድረስ ያሉ እርምጃዎችም ሊወሰዱ እንደሚችሉ ይጠበቃል።ከአውሮፓ ሃገራት ውስጥ በወረርሺኙ ክፉኛ የተጠቃችው ጣሊያን የእግርኳስ ውድድሮቿ በዝግ ስታዲየም እንዲደረጉ የወሰነችው ቀደም ብላ ነበር። ከጣሊያን በመቀጠልም ፈረንሳይ ከ1000 ሰዎች በላይ የሚገኙባቸው ስፖርታዊ ኩነቶች በዝግ እንዲሆኑ ስታደርግ ስፔን፣ ቤልጂየም፣ ጀርመን እና ሌሎች ሃገራትም ይህንኑ ለመተግበር ወስነዋል። የእንግሊዝ እግርኳስ ማህበር እና ፕሪምየር ሊጉ ግን ውድድሮችን እንደቀድሞው ለማስኬድ በመወሰን መርሃግብሮችን ሲያስቀጥሉ ተስተውሏል። በነዚህ ሃገራት ክለቦች የሚጫወቱ ተጫዋቾች፣ አሠልጣኞች እና የክለብ አመራሮች በቫይረሱ መያዝ፣ የበርካታ ክለቦች አባላትም በከፊልም ሆነ በሙሉ በመለያ ክፍሎች (Isolation Rooms) እና በቤት ውስጥ ራስን በመለየት (Self Isolation) ላይ መሆናቸው ግን ሃገራቱ ሊጎቻቸውን በጊዜያዊነት ቢያንስ እስከ ሚያዝያ ወር ድረስ እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል።የሃኖቨር 96ቱ ተከላካይ ቲሞ ሁበርስ፣ የቼልሲው አማካይ ካለም ሃድሰን-ኦዶይ፣ የሳምፕዶሪያው አጥቂ ማኖሎ ጋቢያዲኒ፣ የጁቬንቱሱ ዳኔሌ ሩጋኒ፣ የአርሰናሉ አሠልጣኝ ሚኬል አርቴታ፣ የኦሊምፒያኮስ እና ኖቲንግሃም ፎረስት ክለቦች ባለቤት ኢቫንጀሎስ ማሪናኪስ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው በምርመራ ከተረጋገጡ የእግርኳስ ሰዎች ውስጥ ይጠቀሳሉ።በሃገረ አሜሪካ የእግርኳስ ውድድሩ ሜጀር ሊግ ሶከር ለአንድ ወር ያህል እንዲቆም ሲደረግ ከቅርጫት ኳስ እና አሜሪካን ፉትቦል ጀምሮ የቴኒስ እና የጎልፍ ውድድሮች፣ የቦክስ ግጥሚያዎች፣ የሞተር ሬሲንግ፣ ቤዝቦል፣ የፈረስ ውድድር፣ የኮሌጅ ፉትቦል እና ሌሎች በርካታ ስፖርታዊ ውድድሮች፤ ከዚህም አልፎ እንደ WWE ሬሲሊንግ ያሉ ስፖርታዊ የመዝናኛ ዝግጅቶች በከፊል እንዲቆሙ ሆኗል።ዓለምአቀፍ ስፖርታዊ ዝግጅቶችን ስንመለከት ደግሞ የ2020ው የቶክዮ ኦሊምሊክ እስካሁን 701 የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች እና 10 ከበሽታው ጋር የተያያዙ ሞቶች በተመዘገቡባት ጃፓን እንደመካሄዱ በርካታ አካላት ስጋታቸውን እየገለፁ ቢሆንም ዓለምአቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ ግን ውድድሩን ቀድሞ በተቀመጠው መርሃግብር ለማድረግ እንደተዘጋጀ ገልጿል። ኮሚቴው በመግለጫው ብሏል።በአውሮፓ የሚገኙ ክለቦች ባለፉት ሳምንታት በደጋፊ ፊትም ሆነ በዝግ ስታዲየም ውድድሮችን እያከናወኑ ሲቆዩ የኮሮና ቫይረስን ስርጭት ይከላከላል ብለው ያሰቧቸውን ልምዶች ሲተገብሩ ቆይተዋል። አብዛኛዎቹ ክለቦች ተጫዋቾቻቸው ከደጋፊዎች ጋር ፎቶ ለመነሳትም ሆነ ፊርማቸውን ማኖር እንዳይገናኙ የከለከሉ ሲሆን በርካታዎቹም ከእግርኳሳዊ ኩነቶች (ልምምዶች እና ጨዋታዎች) ውጪ ሌሎች የቡድኑ አባላትን ከህብረተሰቡ ጋር የሚያገናኙ ዝግጅቶችን እና የስታዲየም ጉብኝቶችን አግደዋል፤ እጅግ አስፈላጊ ከሆኑ ሰራተኞች ውጪ ሌሎች ሰዎች በስታዲየሞች እና የልምምድ እና ቴክኒካል ስፍራዎች ላይ እንዳይገኙም አድርገዋል። እንደ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ያሉ ውድድሮች ደግሞ ከጨዋታ በፊት የሚደረገውን የተቃራኒ ቡድን ተጫዋቾች እጅ መጨባበጥ የከለከለ ሲሆን ተጫዋቾችን አጅበው ወደ ሜዳ የሚገቡ ህፃናቶች ልምድም ላልተወሰነ ጊዜ እንዲቆም ሆኗል። ክለቦችም የሊጉን መሪነት በመከተል በልምምድ ሜዳዎች እና በክለብ ቢሮዎች ዙሪያ እጅ መጨባበጥ እንዳይኖር አድርገዋል።ስለ ኮቪድ-2019 ወረርሽኝ መረጃ የሚሰጡ ፖስተሮችን በስታዲየም በመለጠፍ፣ በስታዲየም ስክሪኖች ላይም ትምህርታዊ የሆኑ ምስሎች እንዲተላለፉ በማድረግ ተመልካቾች ስለ በሽታው እንዲያውቁ እና ራሳቸውን እንዲጠብቁ ጥረት ያደረጉ ክለቦችም ነበሩ። በስታዲየም እና የልምምድ ስፍራዎች የፀረ-ቫይረስ እና ፀረ-ባክቴሪያ ኬሚካል ርጭት ማከናወን እና የእጅ ማጠብያ አልኮሎችን በእነዚህ ቦታዎች በማስቀመጥ ህብረተሰቡ እንዲጠቀም ማድረግ በሽታውን ለመከላከል በክለቦች የተወሰዱ እርምጃዎች ነበሩ። ክለቦቹ ማንም ደጋፊ እንደ ሳል፣ ትኩሳት፣ የጉሮሮ ህመም እና ትንፋሽ ማጠር አይነት ምልክቶችን የሚያሳይ ከሆነ ጨዋታዎችን ለመመልከት ወደ ስታዲየሞች እንዳይመጣ ሲማፀኑም ተስተውሏል።የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ከ70 ዓመት በላይ ዕድሜ ያላቸው ደጋፊዎች ወደ ስታዲየም እንዳይመጡ ለማገድ እንቅስቃሴ እያደረገም እንደነበር ተሰምቷል። ይህም የሆነው እነዚህ አረጋውያን በበሽታው የመያዝ እና ከተያዙም በኋላ ወደ ከፍተኛ ህመም፣ አልፎም እስከ ሞት የመድረሳቸው ዕድል ከሌላው የህብረተሰብ ክፍል አንፃር ከፍተኛ በመሆኑ ነው። በእንግሊዝ በተለይም ለአርሴናሉ አሠልጣኝ ሚኬል አርቴታ ለቫይረሱ መጋለጥ ተጠያቂ ነው የተባሉትን ከጨዋታ በፊት እና በኋላ የሚደረጉ ፕሬስ ኮንፈረንሶችንም ላልተወሰነ ጊዜ ለማቆም በዕቅድ ደረጃ ተይዟል።የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር በዛሬው ዕለት በሃገራችን የመጀመሪያውን በላብራቶሪ የተረጋገጠ የኮቪድ-2019 ተጠቂ ይፋ አድርጓል። ይህ ታካሚው ከሳምንት በፊት ከቡርኪና ፋሶ ወደ ሃገራችን የገባ የ48 ዓመት ጃፓናዊ ዜጋ እንደሆነ እና በለይቶ ማከሚያ ማዕከልም በህክምና እየተረዳ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ ጨምሮ አስታውቋል።በሃገራችን የሚኖረው ትክክለኛ የቫይረሱ የስርጭት መጠን ምናልባትም በቀጣይ ሳምንታት ግልፅ እየሆነ የሚመጣ ይሆናል። የበሽታው ስርጭት ከፍተኛ ስጋት ላይ የሚጥል ከሆነም ህብረተሰቡን ከህመሙ ለመጠበቅ ሲባል በርካታ እርምጃዎች ሊወሰዱ ይችላሉ። በአፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ደጋፊ በሜዳ ተገኝቶ ይከታተላቸዋል ከሚባሉ ውድድሮች የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግም ሆነ በዝቅተኛ እርከን ላይ የሚገኙት ሊጎቻችን የእነዚህ እርምጃዎች አንድ አካል ሊሆኑ የሚችሉበት ዕድል ሰፊ ነው። ከላይ የገለፅናቸው የዓለማችን ክለቦች፣ ሊጎች እና የእግርኳስ ማህበራት በሽታውን ለመከላከል የወሰዷቸው እርምጃዎች በአመዛኙ በሃገራችን ተግባራዊ ለመሆን ቢችሉም ከነባራዊ ሁኔታችን አንፃር ከአቅም በላይ የሚሆኑ እንደሚኖሩም ግልፅ ነው።በቂ መፀዳጃ ቤት እና እጅ መታጠቢያ እና ንፁህ የአየር ዝውውር እንኳን የሌላቸው የሃገራችን ስታዲየሞች ዋነኛ የቫይረሱ ስርጭት ማዕከሎች እንዳይሆኑ ቅድመ-ጥንቃቄዎችን ማድረግ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው። ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በቂ የጤና መሰረተ ልማት እና ጠንካራ የፋይናንስ ክንድ ያላቸውን ሃገራት ተሞክሮ ከሃገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማገናዘብም ጨዋታዎችን በዝግ ስታዲየም ከማድረግ አንስቶ እግርኳሳዊ ውድድሮችን እስከማቋረጥ ድረስ የተለያዩ አስፈላጊ እርምጃዎችን የምንወስድባቸው የራሳችን ልኬቶች (thresholds) ያስፈልጉናል። ክለቦች፣ አዲሱ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጋራ ኩባንያ እና ፌዴሬሽኑም ከጤና ተቋማቶቻችን ጋር በመወያየት ሊከሰት ለሚችል ማንኛውም የጤና ስጋት ተገቢውን ውሳኔ እንዲያስተላልፉበት የሚረዳቸውን ቅድመ-ዝግጅት ቢያደርጉ እንመክራለን።", "passage_id": "b5f26c995b47fd1ffa0bea6b1a65cd43" }, { "passage": "የሩሲያዋ\nክራስክኖያስክ የተሰኘች ከተማ ሽር ጉድ ስትልለት የቆየችውን ሻምፒዮና ለመጀመሪያ ጊዜ አካሂዳለች። ስፖርት ወዳዶች ይህንን ሲመለከቱ መቼም «በየትኛው ስፖርት ይሆን?» የሚል ጥያቄ ማንሳታቸው አይቀርም። በእርግጥ ውድድሮች ከስፖርት ባሻገርም በተለያዩ ዘርፎች መዘጋጀታቸው አይቀርም። ይህንን የውድድር ዓይነት ሲያውቁ ግን መሳቅዎና መደነቅዎ አይቀርም (በእኔ ይሁንብዎ)። ይህ\nውድድር ከተለመደው የተለየ ሲሆን፤ ለመሳተፍ በስፖርት ሜዳ እና ጂምናዚየሞች አድካሚ ልምምድ መስራት እንዲሁም የስፖርት ትጥቅና ቁሳቁስ ይዞ መቅረብ አይጠበቅም። በውድድሩ ለመሳተፍ ጉንጭዎን ማጠንከረና እጅዎን ለሰላ ጥፊ ማዘጋጀት ብቻ ነው ያለብዎ። ከዚያማ የመማታትና የጭካኔ ልምድና ችሎታዎን ተጠቅመው ተፎካካሪዎን መጠፍጠፍ ብቻ ነው። አሁን ነገሩን የተረዱት ይመስለኛል፤ የሩሲያዋ ከተማ ያሰናዳችው የጥፊ ሻምፒዮና ነው። ይህ ውድድር በህዝቡ ዘንድ የተወደደ ሲሆን፤ ያለፈው ዓመት ልክ በዚህ ወቅት በሞስኮ ተካሂዶ እንደነበረ የኦዲቲ ሴንትራል ዘገባ ያሳያል። ያኛውን ሻምፒዮና የሚለየው ግን አካላቸውን ለዚሁ ሲሉ ባዳበሩ ስፖርተኞች መካከል መካሄዱ፤ ይሄኛው ደግሞ ፍላጎቱ ባላቸው መካከል በመሆኑ ነው። አዘጋጆቹ እንዳስታወቁት ከሆነም ይህንን ውድድር ለማዘጋጀት ያነሳሳቸው ፍላጎቱ ላላቸው ሰዎች እድሉን ለማመቻቸት ሲሉ ነው። ውድድሩ እንዲህ ነው፤ ተሳታፊዎች ከተዘጋጀው ጠረጴዛ ፊት ለፊት ይቆማሉ። ከዚያም ተራ በተራ የቻሉትን ያህል ኃይል በማውጣት በጥፊ ይመታታሉ። በዚህ መካከል የአንዱ አመዝኖ ሌላኛውን ማንገዳገድ ከቻለ አሸናፊ ይሆናል። ይህ ካልሆነ ግን ከሶስት ሶስት ጥፊ በኋላ ዳኛው አስቁመው በቴክኒካዊ ብቃታቸውና በሰነዘሩት ኃይል ተመስርተው አሸናፊውን ይለያሉ። ውድድሩ\nእውቅና ያገኘ ባይሆንም ጥቂት ህጎች ግን አሉት። ለአብነት ያህል ጉዳትን ለመቀነስ በሚል በእጅ መዳፍ መማተት አይፈቀድም፣ ከጉንጭ አልፎ ጥፊውን በአይን እና ጆሮ ላይ ማሳረፍም የተወገዘ ነው። እንዲያም ሆኖ ግን ግዙፍ አካልና እንደ አንበሳ የሰፋ መዳፍ ያላቸው ተወዳዳሪዎች ሲገጥሙ ጉንጭን እንደ ወረቀት ስለሚያርገበግቡ ጉዳቱ ሚዛንን ስቶ እስከመውደቅ ያደርሳል። በዚህ አስደናቂ ውድድርም የ28ዓመቱና 168 ኪሎ ግራም የሚመዝነው አርሶ አደር ቫስሊ ካሞቴስኪ ሻምፒዮን በመሆኑ የ470ዶላር ተሸላሚ ሆኗል። ይህ ዜና በመገናኛ ብዙሃን ከፍተኛ ሽፋን ካገኘ በኋላም የውድድሩ አዘጋጆች በሌሎች ውድድሮች ላይም ተሳታፊ እንዲሆን ግብዣ እንዳቀረቡለትም ነው የገለጸው።አዲስ\nዘመን መጋቢት 16/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "fdc2e368251d0ac8fdd811889a389902" }, { "passage": " ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪመየር ሊግ አዲስ ውሳኔ ካላስተላለፈ በቀር በተያዘው ወር መጨረሻ ዳግም ወደ ውድድር ለመመለስ ማቀዱ ይታወቃል፡፡ ይህንን ተከትሎም ማንቸስተር ዩናይትድ ከቀናት በኋላ ልምምድ ይጀምራል:: ታዲያ ተጫዋቾች ከአቋማቸው ላለመውረድ በቤታቸው ሆነው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ ማተኮራቸውን በተለያዩ ጊዜያት ለደጋፊዎቻቸው በሚያጋሩት ተንቀሳቃሽ ምስል ያስመለክታሉ፡፡ ይህ ሁኔታም ቀድሞ ለረጅም ሰዓታት አብረዋቸው ያሳልፉ ለነበሩትና አሁን ግን በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች መልዕክት ለሚለዋወጡት አሰልጣኞች መልካም መሆኑን የቀያዮቹ አሰልጣኝ ኦሊጉነር ሶልሻየር ለኢቭኒንግ ስታንዳርድ ገልጸዋል፡፡ ተጫዋቾች ጤናቸውንና አቋማቸውን በመጠበቁ ሂደት ቤተሰቦቻቸውም እንዲያግዟቸው ጭምር ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተዛመተ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ሳቢያ በርካታ ስፖርታዊ ክንዋኔዎች መታገዳቸውን ተከትሎ ስፖርተኞች ከቤታቸው እንዳይወጡ በመከልከላቸው በቤታቸው ሆነው በተለያዩ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲያሳልፉ አስገድዷቸዋል፡፡ በተንቀሳቃሽ ምስል ሁሉም ከገዳዩ ቫይረስ ራሱን እንዲጠብቅ መልእክት በማስተላለፍና ቫይረሱን ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት ድጋፍ ከማድረግ ባለፈም በቤታቸው ውስጥ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በምን መልኩ እንደሚሰሩ ለሌሎች በማስመልከት ላይም ይገኛሉ፡፡ ከተራዘሙ ውድድሮች መካከል አንዱ ኦሊምፒክ እንደመሆኑ በብሄራዊ ቡድን የተካተቱ ስፖርተኞችም ለአንድ ዓመት በምን መልኩ ብቃታቸውን ጠብቀው መቆየት እንደሚችሉ ልምዳቸውን እያካፈሉ ይገኛሉ፡፡ እንግሊዛዊቷ የሁለት ጊዜ የወርልድ ቴኳንዶ የዓለም ቻምፒዮናዋ ጃዴ ጆንስ ለኦሊምፒኩ በተሻለ ብቃት ለመመለስ በአንድ ዓመት መራዘሙን እንደ መልካም አጋጣሚ የምትመለከተው መሆኑን ትገልጻለች፡፡ ውድድሮች፣ የልምምድ አካዳሚዎች እንዲሁም ጂምናዚየሞች በዚህ ወቅት የተዘጉ ቢሆንም በቤት ውስጥ ልምምድ በማድረግ በስፖርቱ የሶስት ጊዜ ቻምፒዮን በመሆን ታሪክ ለመስራት እየተዘጋጀችም ትገኛለች፡፡ ከዚህም ባሻገር ወቅቱን እንደማገገሚያ ጊዜ በመውሰድ ያለመዘናጋት ልምምድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን እንደገለፀች ዘ ጋርዲያን በዘገባው አስነብቧል፡፡ ሌላኛዋ ዋናተኛም በተመሳሳይ የራሷንና የሌሎችን ህይወት አደጋ ላይ ላለመጣል በቤቷ መሆንን አማራጭ የሌለው መሆኑን ታምናለች፡፡ የአምስት ጊዜ ኦሊምፒክ ቻምፒዮናዋ ኬት ሌዴኪ ከሲኤንኤን ጋር በነበራት ቆይታ ከዓመት በኋላ በሚካሄደው ኦሊምፒክ በደካማ አቋም ላለመሳተፍ ልምምዱን በጎረቤቶቿ መዋኛ ገንዳ ላይ አጠናክራ መቀጠሏን ገልጻለች፡፡ በእርግጥ ለ800 ሜትር ነጻ ዋና ቻምፒዮናዋ ልምምድ የምታደርግበት ገንዳ በቂ ባይሆንም ከአቋሟ ዝንፍ ብላ ላለመገኘት ስትል በልምምድ ላይ ትቆያለች፡፡ አንጋፋው ህንዳዊ የስፖርት ጋዜጠኛ ሮሂት ብሪጅናዝ በበኩላቸው ስፖርቱ ሲመለስ የተሻለ ነገር ማግኘት ይሻል ይላሉ፡፡ በቤት ውስጥ መቆየት አስፈላጊ በሆነበት በዚህ ወቅት ውድድሮች ባይኖሩም ከዚህ ቀደም የተካሄዱ ውድድሮችን እንዲሁም ዘጋቢ ፊልሞችን በመመልከት እያሳለፉ መሆኑን ዘ ስቴር ታይምስ አስነብቧል፡፡ በኢትዮጵያም ከዚህ ቫይረስ መስፋትን ተከትሎ ክለቦች፣ ማሰልጠኛ ማዕከላት እንዲሁም ብሄራዊ ቡድኖች ስፖርተኞቻቸውን እንዲበትኑ ተደርጓል:: ስፖርተኞቹ በቡላቸው ባላቸው አቅም ቫይረሱን ለመቆጣጠር በሚደረገው ርብርብ ከደጋፊዎቻቸውና በተናጥል በመሆን ድጋፍ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን ብቃታቸውን ጠብቀው ለመቆየት ምን እያደረጉ እንደሆነ መረዳት አልተቻለም፡፡ ስፖርተኛ ሁሌም ብቁና ዝግጁ ሆኖ መገኘት ያለበት እንደመሆኑ ከሌሎች ተሞክሮ በመውሰድ ይህንን በቤት ውስጥ የማሳለፍ ወቅት አቅማቸው በቻለ መጠን ዝግጅታቸውን ማከናወን ተገቢ መሆኑን የስፖርት ባለሙያዎችም ይመክራሉ፡፡ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ስፖርተኞች በየግላቸው ጊዜውን እንዲያሳልፉና መመሪያዎችን መከተል እንደሚገባቸው በመግለጫው ጠቁሟል፡፡ በሌላ በኩል በአትሌቲክስ ስፖርት የምትታወቀው ኢትዮጵያ አትሌቶች ከአበረታች መድሃኒት የጸዳ ጊዜ ማሳለፍ እንደሚገባቸው ተመልክቷል፡፡ ብሄራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ጽህፈት ቤት አትሌቶች ሳይዘናጉ ራሳቸውን እንዲጠብቁና በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ያልተገባ ጥቅምን ለማግኘት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የህግ ጥሰት በሚፈጽሙት ላይ የእርምት እርምጅ ይወሰዳል፡፡ ከዚህ ቀደም ይከናወን የነበረው የአትሌቶችን ናሙና የመውሰድና የመመርመር ሂደትም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጽህፈት ቤቱ አሳስቧል፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 24/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "21899956b5d85efbc79462ca38c89e30" } ]
3a339ddab883c846be3063016e19c43f
2feeef4d19d76b7f12172cbc68c24aae
ሥራ ላይ ያልዋሉ ማዘውተሪያ ስፍራዎች በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገቡ ጥረት እየተደረገ ነው
በኢትዮጵያ ከ27 ሺ በላይ የጥርጊያ ሜዳዎች እንዲሁም 12 ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች መኖራቸውን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በሥራ ላይ ያልዋሉ ማዘውተሪያ ሥፍራዎችን በፍጥነት ወደ ሥራ ለማስገባትም ኮሚሽኑ ጥረት እያደረገ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ አገሪቷ በስፖርት ዘርፍ ትኩረት ሰጥታ ከምታከናውናቸው ሥራዎች መካከል አንዱ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ነው፡፡ በቅርቡ የማዘውተሪያ ስፍራዎች የወጣውን የመተዳደሪያ ደንብ ተከትሎ በተደረገው ቆጠራ በዚህ ወቅት ከ27 ሺ በላይ የጥርጊያ ሜዳዎች በአገሪቷ የሚገኙ መሆኑን ኮሚሽኑ ጠቁሟል፡፡ ግንባታቸው ሙሉ ለሙሉ ያልተጠናቀቁና አንዳንዶቹም የስታንዳርድ ችግር ያለባቸው ቢሆኑም በአገሪቷ ውስጥ የሁለተኛ ምዕራፍ ግንባታው የተጀመረውን ብሄራዊ ስታዲየም ጨምሮ 12 ትልልቅ ስታዲየሞች ይገኛሉ፡፡ ይህም በክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገነቡት አጠቃላይ ስታዲየሞች ቢደመሩ መንግሥት ከፍተኛ ወጪ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ የሚያሳይ መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ገልጸዋል፡፡ መንግሥት በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከትንንሽ እስከ ትልልቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ እያወጣ ቢሆንም በተለያዩ አካባቢዎች በተገቢው ጊዜ ተጠናቀው ወደ ሥራ ያልገቡ አሉ፡፡ በመሆኑም በፍጥነት ወደ አገልግሎት ማስገባት አስፈላጊ በመሆኑ ተጀምረው በወቅቱ ያልተጠናቀቁና ጥራታቸውን ያልጠበቁ ግንባታዎች በፍጥነትና በጥራት እንዲጠናቀቁ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡ ፡ የካፍና የፊፋን መስፈርት የማያሟሉትም ለማሟላት ጥረት እያደረጉ፤ ክልሎችም ሃብት መድበው ርብርብ እያደረጉ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ በኮሚሽኑ ስር ያሉትንም በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ ለማስገባት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ በሲኤምሲ አካባቢ 31ሺ ካሬ ሜትር ቦታ በስፖርት ኮሚሽን የተያዘና ለውሃ ዋና እና ለቴኒስ ስፖርቶች ማዘውተሪያ የሚውል ቦታ አንዱ ነው፡፡ በመሆኑም በቅርብ ቀን ጨረታ አውጥቶ የማጠር እንዲሁም በቀጣይ ዓመት ወደ ግንባታ ለመግባት ታቅዷል፡፡ በተመሳሳይ በዚያው በሲኤምሲ አካባቢ ካፍ የገነባው ትልቅ ማዕከል ቢኖርም ለብዙ ጊዜ አገልግሎት ሳይሰጥ ቆይቷል፡፡ ማዕከሉ ስታንዳርዱን የጠበቀ ቢሆንም ብዙ ጊዜ ብሄራዊ ቡድን ለማሳረፍ ችግሮች እንዳሉበት ይነሳል፡፡ በመሆኑም ማዕከል በቅርቡ ወደ ሥራ እንዲገባ ይደረጋል፡፡ ለረጅም ጊዜ በብቸኝነት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው አዲስ አበባ ስታዲየም ተጎድቷል፡፡ በመሆኑም በጀት ለሚመለከተው አካል በማቅረብ በክረምት ወቅት እድሳትና ጥገና በማድረግ በድጋሚ ዓለም አቀፍ ጨዋታዎችን ማድረግ እንዲችል ጥረት የሚደረግ መሆኑን ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው አሳውቀዋል፡፡ እንደ ማዘውተሪያ ስፍራዎች በአጠቃላይ ያለው ሁኔታ ሲታይ መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠው ዘርፍ ነው፡፡ ከቀበሌ ጀምሮ ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንዲሆኑ የተዘጋጁ ስፍራዎች በከፍተኛ ደረጃ ኢንቨስትመንት ሊካሄድባቸው የሚችሉ ናቸው፡፡ ስፖርቱ የልማቱ አንድ አካል፤ ህብረተሰቡም በስፖርታዊ እንቅስቃሴ መሳተፍ መብቱ በመሆኑ በሚመለከታቸው አካላት ያለው የመሬት አቅርቦት መልካም የሚባል ነው፡፡ በቅርቡ በተዘጋጀው ብሄራዊ የስፖርት ሪፎርም ላይ በጉልህ ከተመላከቱ ጉዳዮች መካከል አንዱ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ልማት ነው፡፡ ከማዘውተሪያ ስፍራዎች ጋር በተያያዘ የስፖርት ፖሊሲው ሲቀረጽ እንደ ጉድለት የተያዘው አንዱ የመተዳደሪያ አዋጅ አለመኖሩ ነው፡፡ በቅርቡ ደንብ መውጣቱን ተከትሎም እነዚህ ሜዳዎች ‹ስታንዳርዱን ያሟሉ፣ የይዞታ ማረጋገጫ አላቸው፣ ጥራትና ተደራሽነታቸው ከፍላጎቶች አንጻር ተገቢ ነው፡፡ እንዲሁም ሥራ ላይ ውለው ማህበረሰቡ እየተገለገለባቸው ነው?› የሚለው ዋነኛው ጥያቄ ነው፡፡ በመሆኑም ለጥያቄዎቹ ምላሽ ሊሰጡ የሚችሉ ሥራዎች በኮሚሽኑ በኩል በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ነው ኮሚሽነሩ የጠቆሙት፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 26/2012ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29780
[ { "passage": "የአዲስ አበባ ስታዲየም የዕድሳት ሥራ ለማከናወን የዲዛይን፣ የማማከር እና የቁጥጥር አገልግሎት ከሚሠራ ድርጅት ጋር የውል ስምምነት መደረጉን የስፖርት ኮሚሽን አስታውቋል ።የዲዛይን፣ የማማከርና የቁጥጥር አገልግሎቱን የሚያከናውነው ዮሐንስ ዓባይ አማካሪ አርክቴክቸር እና ኢንጅነሪንግ በተባለ ድርጅት ሲሆን የዲዛይን ስራውን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ የሚያቀርብ ይሆናል። የዲዛይን ሥራው የካፍ ስታንዳርድን ጠብቆ እንደሚሰራ ለማወቅ ተችሏል።72 ዓመታት ያስቆጠረው የአዲስ አበባ ስታዲየም በዕድሜ ብዛት ዘመኑን የሚመጥን ስላለመሆኑ በተደጋጋሚ ሲነገር የቆየ ሲሆን ካፍ ዓለምአቀፍ ውድድሮች እንዳይደረጉበት ማገዱ ይታወሳል። ዘንድሮ 36 የሊግ እና አራት ኢንተርናሽናል ጨዋታዎች ያደረገው ስታዲየሙ መጠነ ሰፊ እድሳት ከተደረገለት ረጅም ዓመታት አልፈውታል።", "passage_id": "91b0b1d61e82ce61fa25f873c11fef41" }, { "passage": "ለወጣቶች ሥራ ፈጠራ የተሰጡ የመሥርያና የመሸጫ ቦታዎች (ሼድዎች) ኦዲት እየተደረጉ መሆኑን፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) አስታወቁ፡፡ምክትል ከንቲባው ከአዲስ አበባ ወጣቶች ጋር የሚያካሂዱትን ውይይት በመቀጠል፣ ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ጋር ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ተወያይተዋል፡፡ወጣቶቹ ለከንቲባው ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል ለሥራ ፈጠራ የተሰጡ ሰፋፊ ቦታዎች በሕገወጥ መንገድ ለሦስተኛ ወገን ተላልፈው መሰጠታቸው፣ በተለያዩ ቦታዎች ለፓርክ ተብለው የተዘጋጁ ቦታዎች ታጥረው በማይገባቸው አካላት መያዛቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ምክትል ከንቲባው ለተነሱት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ፣ በከተማ አስተዳደሩ ወጪ የተሠሩ ሼዶች ኦዲት እየተደረጉ ነው ብለዋል፡፡‹‹ሼድ ወስደው ያከራዩና በሕገወጥ መንገድ የያዙ በኦዲት ግኝቱ ይለያሉ፤›› ያሉት ምክትል ከንቲባው፣ ‹‹የኦዲት ሥራው እንደተጠናቀቀ ሼዶቹ ለሚገባቸው ወጣቶች እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡በከንቲባ ድሪባ ኩማ የሥልጣን ዘመን ለወጣቶች ሥራ ፈጠራ አገልግሎት የሚውሉ በአሥር ሺሕ ካሬ ሜትር የሚለኩ የመሥሪያና የመሸጫ ቦታዎች ለወጣቶች ተላልፈው መሰጠታቸው ይነገር ነበር፡፡ነገር ግን ወጣቶች በተለያዩ ጊዜያት ባቀረቡት ቅሬታ አብዛኞቹ ሼዶች የተሰጡት ለሚገባቸው ወጣቶች አይደለም ይላሉ፡፡ ይልቁኑም በኪራይና በተለያዩ መንገዶች ለሦስተኛ ወገን ተላልፈው ተሰጥተዋል ሲሉም ያማርራሉ፡፡የወጣቶቹን ጥያቄ የተቀበለው የምክትል ከንቲባ ታከለ ካቢኔ ሼዶቹ ኦዲት እንዲደረጉ የወሰነ ሲሆን፣ ከኦዲት ግኝቱ በኋላ ምላሽ እንደሚሰጥና ወጣቶቹም ያላቸውን ማስረጃ በማቅረብ እንዲተባበሩ ጠይቋል፡፡ከዚህ በተጨማሪ በከተማው የተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ ፓርኮች ያላግባብ የተያዙና በትክክለኛው መንገድ አገልግሎት እየሰጡ አለመሆኑ ተወስቷል፡፡ምክትል ከንቲባው በዚህም ላይ በሰጡት ምላሽ እንዳሉት፣ በከተማው የሚገኙ ፓርኮች በየትኛውም አካል የተያዙ እንኳ ቢሆን ዕርምጃ ተወስዶ ለወጣቶች ይተላለፋሉ፡፡ይህንንም ለማስፈጸም በተለያዩ መዋቅሮች የሚገኙ አመራሮች በትኩረት እንዲሠሩ ምክትል ከንቲባው የቃል መመርያ መስጠታቸው ታውቋል፡፡በአዲስ አበባ ከተማ የለሙ አሥር ፓርኮችና በቀድሞው ማስተር ፕላን ለፓርክ አገልግሎት የተመደቡ 16 ፓርኮች ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን ፓርኮቹ በአግባቡ አገልግሎት እየሰጡ አለመሆኑ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡", "passage_id": "54809aee4c9aa92664c5550a01a54423" }, { "passage": "ግንባታው ከተጀመረ ዘጠኝ ዓመታትን ያስቆጠረው የሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተለያዩ ምክንያቶች እየተጓተተ ለምን እስካሁን መጠናቀቅ አልቻለም?በ2004 ግንባታው የተጀመረውና ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ከ45-50 ሺህ ተመልካቾችን በወንበር እንደሚያስተናግድ የተነገረለት ስታዲየሙ በአራት ዓመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ቢጠበቅም በተለያዩ ምክንያቶች እየተጓተተ ዓመታት ተቆጥረው እስካሁን መጠናቀቅ አልቻለም፡፡ በ2008 ለመላው ኢትዮጵያ ውድድሮች ሲባል አፋጣኝ ሥራዎችን ሲከወን የነበረው የዚህ ስታዲየም ፕሮጀክት ከውድድሩ በኋላ ግን ያዘገመ ሥራዎች እየተሰሩበት አሁን ላይ “ቆሟል” የሚባልበት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ሳትኮም በተባለ የኮንስትራክሽን ተቋራጭ ሲሰራ የቆየው ስታዲየሙ ባልተጠናቀቀበት ሁኔታ ከሀገር አቀፍ ስፖርታዊ ጨዋታዎች አንስቶ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወላይታ ድቻ ክለቦች አህጉራዊ ውድድሮች ግልጋሎት ሰጥቷል። ስታዲየሙ በውድድር ወቅት በተለይ እንደ ችግር የሚነሳበት የመጫወቻ ሳሩን የመቀየር ሥራ በስድስት ወራት ውስጥ ተፈፃሚ ይሆናል ተብሎ ቢጠበቅም ወቅቱን መጠበቅ ሳይችል ይኸው ድፍን ሁለት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ የመብራት (ፓውዛ)፣ ስክሪን ገጠማ፣ የሚዲያ ክፍል፣ የመልበሻ፣ የውስጥ ማማሟቂያ እና መፀዳጃ ቤቶች የተሰሩለት ቢሆንም የወንበር፣ የተጠባባቂ ተጫዋቾች መቀመጫ፣ ጥላ፣ መጠነኛ ማሻሻያን የሚሹ የዲዛይን ሥራዎች እንዲሁም የፊኒሺንግ ሥራዎች ይጠብቁታል። ከዚህም በተጨማሪ ከሜዳው ውጪ የሚገኙ ሁለት የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳዎች እና በዲዛይኑ ላይ የተካተቱ የሌሎች ስፖርቶች ማከናወኛ ግንባታዎች ከዚህ ቀደም በጥንድፊያ የተሰሩ በመሆናቸው በዲዛይኑ መሠረት መጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል።የደቡብ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ የሺዋስ ዓለሙ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ ስታዲየሙ አሁን ያለበት ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን በዚህ መልኩ አስረድተዋል።“በመጀመሪያው ዙር ግንባታ በአመዛኙ ትልቁ ስታዲየም መሠረታዊ ሥራዎች እያለቁ ነው። ችግር የነበረበት የሳር ንጣፉ አሁን እየተስተካከለ ነው። ከዛ ውጪ ያለው የቴክኖሎጂ ገጠማው ነው፤ እሱ የኮንስትራክሽን ድርጅቱ ሳትኮም ያመጣው የውጪ ድርጅት ጋር በመሆን አብዛኛዎቹን የቴክኖሎጂ ሥራዎችን ጨርሷቸዋል፡፡ ባለፈው ህዳር እና ታኅሣሥ ላይ የቴክኖሎጂ ገጠማ ሥራው ተሰርቷል፡፡ በሁለተኛ ምዕራፍ የተያዘው የጣራ እና የወንበር ሥራ ነው የሚቀረው። እሱ በኮንትራክተሩ እና በክልላችን ኮንስትራክሽን ቢሮ አማካኝነት አዲስ የተሰራ ዲዛይን ስላለ ዲዛይኑ ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ ተብሎ የማሻሻያ ሥራው እየተሰራ ነው። ይህ የዋናውን የስታዲየም ገፅታ የተመለከተ ጉዳይ ነው።“ከዚህ ጋር ተያይዞ ካፍ በተደጋጋሚ የሰጣቸው ኮመንቶች አሉ። በተሰጡን ኮመንቶች መሠረት ከማስተካከል አኳያ አንዳንዶቹ ከመጡት ገምጋሚ ቡድን ጋር ካለ የመረጃ ልውውጥ ችግር ጋር የተያያዘ ነው። ያ ደግሞ ሰነዶች ከታዩ በኃላ ለማስተካከል ተሞክሯል፡፡ የሚቀሩ ክፍሎችን የማደስ መሠረታዊ የሆኑ ሀሳቦች ቀርበዋል። የመጫወቻ ሜዳ፣ የመልበሻ ክፍል፣ የውስጥ ማማሟቂያን በተመለከተ በአመዛኙ በተሰጡት አስተያየቶች መሠረት ለማስተካከል ተችሏል፡፡ ከዋናው ስታዲየም ጋር በተጓዳኝ የማስፋፊያ ሥራዎች ደግሞ አሉ። የመለማመጃ ሜዳ፣ ትንንሽ ሜዳዎች (እንደ ቅርጫት ኳስ ሜዳ እና መሰሎች)፣ ውሀ መዋኛ እና ሌሎች ቀሪ ሥራዎች አሉ። ”ኮሚሽነሩ ሥለ ግንባታው በጊዜው አለመጓዝ ላነሳንላቸው ጥያቄ ማብራሪያቸውን በመቀጠል የበጀት፣ የኮሚቴ መቀያየር፣ ከተቋራጮች ጋር አለመግባባት፣ የፀጥታ ሁኔታ እና ኮሮና ወረርሺኝ ለፕሮጀክቱ መጓተት ምክንያት መሆናቸውን ገልፀዋል።“ሥራውን ከያዘው የኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር አለመግባባት እየተፈጠረ በመሆኑ በአማካሪው እና በአሰሪ ቢሮው በኩልም ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት ነበር፤ ነገር ግን ውጤታማ ባለመሆኑ እያነሳ ያለውም ጥያቄ በአሰራር ደረጃ የማይመለስ በመሆኑ ውሉን ለማቋረጥ እንቅስቃሴ ላይ ነን። የማስፋፊያ ሥራውን የሚሰራው ‘በረከት እንደሻው’ የሚባል ድርጅት ጋር ከ2008 ጀምሮ (የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ጀምሮ) ሲሰራ የነበረ ድርጅት ነው። የሚጠይቃቸው ጥያቄዎችን ከተገባው ውል አንፃር ሊመለሱ የማይችሉ ከመሆኑ ባለፈ ያለፉትን 18 ወራት ሥራ ላይም ስላልነበረ ተገምግሞ የመጨረሻ ውሳኔ ላይ እየተደረሰ ነው ያለው፡፡” ከተቋራጩ በተጨማሪ ፕሮጀክቱን የሚከታተለው ኮሚቴ በየጊዜው መለዋወጥ ሥራውን አስቸጋሪ አድርጎታል። ‘የሀዋሳ ስታዲየም የህዝብ ተሳትፎ እና አስተዳደር’ የሚባል ኮሚቴ አለ። እዚህ ክልል በነበረው የአመራር መለዋወጥ እና ሽግሽግ በአብዛኛውም ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩም በአጠቃላይ አሁን ስለሌሉ ያን የመተካት ጉዳይ ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም እና ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጋር ተነጋግሮ የፈረሰውን ቦርድ መልሶ ለመሰየም እና ለማቋቋም እንቅስቃሴ ላይ ነው ያለነው።” ከዚህ ጎን ለጎን በሁለተኛው ምዕራፍ የሚካተቱ የፊኒሽንግ እና ብዙ ወጪ የሚያስወጣው የጣሪያ፣ የወንበር እንዲሁም ዙሪያ አጥር ግንባታ ለመስራት ባለፈው ክረምት ጨረታ ወጥቶ ነበር። ሆኖም የወጣውን የሚያሟላ አካል ስላልነበር፣ ለዛ የሚረዳ በቂ በጀትም ስላልነበረ በቴክኒክ ውድቅ ተደርጎ ተጨማሪ በጀት ወጥቶ በድጋሚ ጨረታ ለማውጣት ከ200 እስከ 250 ሚሊዮን ያስፈልጋል የሚል መመሪያ ስላለ ያን ለማድረግ በሒደት ላይ ነው ያለነው። ትልቅ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ውድድሮች ሲያስተናግድ የነበረ ሜዳ ቢሆንም በተጠበቀው ልክ ባለፉት ሁለት ዓመታት ሥራ አልተሰራም። ለሥራው የክልሉ መንግሥት በጀት በአግባቡ ሲበጅት ቢቆይም በነበረው የፀጥታ ችግር ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም። በዚህ ዓመት ለመከናወን ሲታሰብ ደግሞ ለግንባታው የተያዙ አብዛኛው ወጪዎች ወደ ኮሮና ስለዞሩ የበጀት እጥረት አጋጥሟል።“የሳር መቀየር ሥራው እንደተባለው መከናወን ከነበረበት ጊዜ አንፃር በጣም ቆይቷል። ወደ መቀየሩ ሒደት ዘንድሮ ነው የተገባው። ግን ችግሩን በጥልቀት ገምግሞ ከማቅረብ አንፃር መዘግየቶች ነበሩ፡፡ አብዛኛው የሜዳውን ስራ የሚይዘው ይሄን ሳር የመቀየር ነው፡፡ ሳሩን ለመቀየርም በዝርዝር ነው እየተገመገመ የሄደው ለዚህ የሚመች ደረጃው የጠበቀ ኮረት የማስተካከል አፈሩን የማጠብ የፍሳሽ ሥርዓቱን የማስተካከል ጉዳይ አሁን በሚገባ እየሄደ ነው ያለው። ከኮንትራክተሩ ጋር የነበረን ውል በዚህ ሚያዚያ ወር ላይ የሚያልቅ የነበረ በመሆኑ በፍጥነት ነው ሲሰራ የነበረው። አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ ጥሩ ነው። ያው የዘገየበት ሁኔታ የአስፈፃሚ አካላት መጓተት አመራሩ በፍጥነት መመሪያ ያለመስጠት ያመጣው ችግር ቢሆንም ዘንድሮ ያን ለማስተካከል ተሞክሯል፡፡ የሳር ንጣፉ በአምስት ወር ለመጨረስ ነው ስምምነት ላይ የተደረሰው። ጥሩ እየሄደ ከኮሮና መምጣት ጋር በተያያዘ ግን ዘግይቷል፡፡ አሁን ግን በፍጥነት ተመልሶ ወደ ስራ እንዲገባ መግባባት ላይ ስለተደረሰ በሁለት ወር የመጨረስ ስራ ላይ እንገኛለን። ችግሩ ተከስቷል፤ ለማስተካከልም ተዘግይቷል። ያም ቢሆን በአጭር ጊዜ ይጠናቀቃል፡፡ ”ስታዲየሙ መቼ እንደሚናቀቅ እና ቀጣይ ሥራዎች በምን መልኩ እንደሚካሄዱ ግልፅ መረጃ ማግኘት አዳጋች ሲሆን ካለው የሀገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር በቂ የማጠናቀቂያ በጀት የማግኘቱ ጉዳይ አጠያያቂ ሆኖበታል። በጉዳዩ ላይም ለስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነሩ ጥያቄውን አንስተን ስታዲየሙን ለማጠናቀቅ እየሄዱ ስላሉበት መንገድ እና እቅድ የሚከተለውን ብለውናል።” ከዋናው ስታዲየም ጋር በምዕራፍ ሁለት መካተት ያለበት የጣሪያ እና የወንበር ሥራ የራሱ የሆነ በጀት ስለሚፈልግ ከመስተዳድር ምክር ቤት እና ከክልሉ ምክር ቤት ጋር ተነጋግሮ ማስመደብ፤ በመቀጠል ባለፉት ሁለት ዓመታት የዘገየውን ስታዲየም በምን አይነት መልኩ እናፋጥነው የሚለው ጉዳይ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተነጋግረን አዲስ ቦርድም ተቋቁሞ ይሄን በበላይነት የሚመራውን ዳግም ለመመለስ በሒደት ላይ ነን።“እንደ ኮሚሽን የመጀመሪያው ምዕራፍ ዘንድሮ መጠናቀቅ አለበት የሚል አቋም ነው የያዝነው። በመጀመሪያው ዙር ቅድም ያልኩት የመጫወቻ ሳሩ ያልቃል፣ የቴክኖሎጂ ገጠማው ያልቃል፣ በዚህ ዙር ተጨማሪ ኮንትራት የተሰጡ የውጪ የማስፋፊያ በአመዛኙ ብዙዎቹ አልቀው የተወሰኑት በኮንትራክተሩ በተፈጠረው ችግሮች የተቋረጡ ቢኖሩም የተሰሩ ሥራዎች ግን አሉ፡፡ ከማስፋፊያ ስራዎች አንፃር 86% ተሰርቷል፡፡ በትልቁ ስታዲየምም ላይ መሰራት ካለበት መሀከል 96% ተሰርቷል፡፡ የማስተካከል እና የለቀማ ስራዎች ሲቀሩ ይሄን ዘንድሮ ለመጨረስም ነው ያሰብነው። የአጥር ግንባታ እና የላንድ ስኬፒንግ ስራ በሚቀጥለው በጀት ዓመት አጋማሽ ላይ እንጨርሳለን የሚል ነው የኮሚሽኑ እቅድ። ”እስከ አሁን 750 ሚሊዮን ብር ፈሰስ እንደተደረገበት የተነገረለት ስታዲየሙን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ለአዲስ የኮንስትራክሽን ተቋራጭ ጨረታ አውጥቶ በቀጣይ ሥራ የሚጠብቀው ሲሆን ዘንድሮ ወደ ሥራ ለመመለስ 20 ሚሊዮን ብር በጀት ቢመደብለትም በተለያዩ ምክንያቶች መንግስት ከዚህ በጀት ላይ 16 ሚሊዮን ብሩን ለሌላ ስራ አውሎታል ተብሏል፡፡ በቀጣይ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅም ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብን እንደሚጠይቅ ታውቋል።", "passage_id": "e6e7e64ab165afacb36b0ee524cf2e98" }, { "passage": "ኮሚሽኑ እንዳለው የወረርሽኙ ስጋት ባለበት ሁኔታ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች መልሰው እንዲጀመሩ ለማድረግ በተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።\n\nየአገሪቱ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት አቶ ኤሊያስ ሽኩር እንደተናገሩት በበሽታው ምክንያት የተቋረጡትን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ከዚህ በላይ እንዲዘገዩ ማድረግ በስፖርት ቤተሰቡ ላይ የሚፈጠረው ጫና ከፍተኛ ነው ብለዋል። \n\nየኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰትን ተከትሎ የበሽታውን መስፋፋት ለመቆጣጠር ሲባል በአገሪቱ ስፖርታዊ ስልጠናዎች፣ ውድድሮች በአጠቃላይ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ተደርጎ ቆይቷል።\n\nበዚህም ሳቢያ የስፖርት ዘርፍ ክፉኛ መጎዳቱን ያመለከተው ኮሚሽኑ፤ ክለቦች የመፍረስ አዳጋ እንደተጋረጠባቸውና የስፖርት ቤተሰቡም የሥነ ልቦና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ መግባታቸውን ገልጿል። \n\nበመሆኑም አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ የስፖርት እንቅስቃሴዎችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችንና የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ መሠረት በማድረግ ረቂቅ መመሪያው ተዘጋጅቶ ውይይት ተካሂዷል።\n\nመመሪያው አጠቃላይ የስፖርት እንቅስቃሴዎች በምን ሁኔታ መከናወን እንዳለባቸው የሚያሳይ ሲሆን የስፖርት ተቋማትና ማኅበራት ከሚያካሂዷቸው ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ባህሪ አንጻር አስፈላጊ የጥንቃቄና የአሠራር ሥርዓት ሊያዘጋጁ እንደሚችሉ እንደሚያመለክት ኮሚሽኑ ገልጿል። \n\nበዚህም መሰረት የስልጠናና የውድድር ስፍራዎች ለበሽታው ያላቸውን ተጋላጭነት ባገናዘበ ሁኔታ ደረጃ በደረጃ በግልና በቡድን አነስተኛ ተሳታፊ ቁጥርን ታሳቢ ያደረገ ሊሆን እንደሚገባ ተቀምጧል። \n\nእንዲሁም ወደ ስልጠናና ወድድር የሚገቡ አካላት ምርመራ ማድረግ፣ የንጽህና መጠበቂያዎችን መጠቀምና ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚያገለግሉ ቦታዎች፣ ቁሳቁሶችና መሳሪያዎች ንጽህናቸው ሊጠበቅ እንደሚገባ መመሪያው ጠቅሷል። \n\nባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የእግር ኳስ ውድድርን መልሶ ለማስጀመር እየታሰበ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ውድድሩ ሲጀመር የተመልካቹንና የስፖርተኞቹን ጤና ደኅንነት ያስጠበቀ እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎችን ለማከናወን ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል። \n\nየኮሮናቫይረስ ኢትዮጵያ ውስጥ መገኘቱ ከታወቀ በኋላ ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑና በርካታ ሰው የሚታደምባቸው ስፖርታዊ ውድድሮችን የመሰሉ እንቅስቃሴዎች እንዳይካሄዱ መደረጉ ይታወሳል። \n\n ", "passage_id": "366ae60f019c2f68ce5212abe333968c" }, { "passage": "በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ግንባታቸው እየተጠናቀቀ የሚገኙ የስፖርት መሠረተ ልማት ስፍራዎች በምክትል ከንቲባው የሚመራው የልዑክ ቡድን ከትላት ጀምሮ ሲጎበኙ ውለዋል። ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጅነር) የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት እና ባህልና ቱሪዝም የቢሮ ኃላፊዎች፣ የክለብ ደጋፊዎች እና የሚዲያ አካላት በተገኙበት ነበር ከ08:00 ጀምሮ መጎብኘት የተጀመረው። የጉብኝታቸው የመጀመርያ ስፍራ ከ1992 ጀምሮ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው አበበ ቢቂላ ስታዲየም ሰፊ የእድሳት ስራ ሲሆን አብዛኛው ምዕራፍ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል። ለስቴዲየሙ የተለየ ውበት የፈጠረት ሙሉ የተመልካች መቀመጫ ክፍል የወንበር ግጣሙ ተጠናቆ የተቀሩት ስራዎች ለምሳሌ የመሮጫ ትራኩ የመጀመርያው የኮንክሪት ንጣፉ ተጠናቆ መም (ትራክ) የማልበስ ስራው በጅማሮ ላይ ሲገኝ የስታዲየሙን ሙሉ ክፍል ጣርያ የማልበስ ስራ የብረት ግጣሙ አልቆ ጣሪያው ማልበስ በቅርቡ ይጀመራል ተብሏል። በአጠቃላይ አብዛኛው ስራዎቹ እየተገባደደ እንደሆነና ሚያዚያ ወር መጀመርያ ላይ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር፤ እስካሁን ለእድሳት እና ግንባታው ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደወጣበትም ሰምተናል። በመቀጠል ክቡር ምክትል ከንቲባው ከራስ ኃይሉ ሁለገብ የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራ ጉብኝታቸው በኋላ ያመሩት በአዲስ አበባ ከሚገኙ ስታዲየሞች ሁሉ ተወዳዳሪ ወደሌለው በመንግስት ሙሉ ወጪ ሽፋን ተደርጎለት ከ60 ሺህ በላይ ተመልካች የመያዝ አቅም እንዲኖረው ታስቦ ግንባታው ከሦስት አመት በፊት ወደጀመረው ቦሌ አካባቢ የሚገኘው ዓለም አቀፍ ብሔራዊ ስቴዲየም ነበር። የስቴዲየሙ የግንባታ ቁመናው የተጠናቀቀ ሲሆን የመጫወቻ ሜዳውን እና የመሮጫ ትራኩን ለመስራት በእንቅስቃሴ ላይ እንደሆነ ለማየት ችለናል። ከ65% በላይ ግንባታው የተጠናቀቀ ሲሆን እስካሁን ከፍተኛ የሆነ ወጪ እየወጣበት ሲገኝ ግንባታውን በፍጥነት በማጠናቀቅ በዋናነት በ2020 ኢትዮጵያ ለምታስተናግደው የአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ (ቻን) ለማድረስ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።በመጨረሻም ምክትል ከንቲባው ተዟዙረው በተመለከቱት ነገር መደሰታቸውን በመግለፅ ግንባታቸው በፍጥነት እንዲጠናቀቅ መመርያ የሰጡ ሲሆን በቀጣይ ሌሎች የስፖርት መሠረተ ልማቶችን በአዲስ አበባ ከተማ በስፋት እንደሚገነቡ እና የተወሰዱ የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራዎችን ለማስመለስ እንደታሰበ ተናግረዋል።አስቀድሞ ከጠዋት ጀምሮ የጉብኝታቸው አካል ይሆናሉ ተብለው መርሐ ግብር የወጣላቸው በተለይ የአቃቂ ስታዲየም ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ቡና ስታዲየሞችን በተለያዩ ምክንያቶች እና በፕሮግራም መጣበብ የተነሳ በቅርቡ ለመጎብኘት ቀጠሮ እንደያዙ በመግለፅ ሳይጎበኙ ቀርተዋል።", "passage_id": "ca8247026a1fada22601ca8324817516" } ]
4837c08cf8c005b29cbe0953d63c38d1
1b08f73865713f1e30bc30dc44f23f87
በኮሮና ቫይረስ ሕይወቱን ያጣው የስፖርት ጋዜጠኛ
ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከአንድ ሚሊየን በላይ የዓለምን ሕዝብ ያጠቃው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ያልገባበት ቤት፣ ያላንኳኳው በር የለም። ከዓለም ታላላቅ አገራት መሪዎች እስከ ተራው ሕዝብ፣ ከዝነኛ ሰዎች እስከ ሕፃናትና አዛውንት ድረስ የዚህ አስከፊ ወረርሽኝ ተጠቂ ሆነዋል። ቫይረሱን ለመቋቋም በሽታን የመመከት ከፍተኛ አቅም ያላቸው የስፖርቱ ዓለም ሰዎች ሳይቀሩ በዚህ ወረርሽኝ ተለክፈዋል፣ ሕይወታቸውን ያጡም ጥቂት አይደሉም። የስፖርት ቤተሰቡ በቫይረሱ ስርጭት ስጋት የዓለም ታላላቅ የስፖርት መድረኮች ተቆልፈውበት ሁነኛ የመዝናኛ አማራጩን አጥቶ በየቤቱ ቆዝሟል። የስፖርቱ ዓለም ታላላቅ ከዋክብትም ረብጣ ገንዘብና ዝናቸው ከደጃፋቸው እንዲወጡ አቅም አልሆናቸውም። የኮሮና ቫይረስ በስፖርቱ ዓለምና በስፖርት ቤተሰቡ የሚያሳድረው አሉታዊ ተፅዕኖ በሳምንቱ አጋማሽ ወደ ሃዘን የቀየረ አጋጣሚ ፈጥሯል። ፈረንሳዊው እውቅ የስፖርት ጋዜጠኛ ፔፕ ዲዉፍ ባለፈው ረቡዕ በኮሮና ቫይረስ ምክኒያት ሴኔጋል መዲና ዳካር ውስጥ በስልሳ ስምንት ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የመለየቱ ዜና ተሰምቷል። ይህም በመላው ሴኔጋልና አፍሪካ እንዲሁም ፈረንሳይ ትልቅ የስፖርቱ ዓለም አሳዛኝ ክስተት ሆኗል። ትውልዱን በቻድ አቢቼ ያደረገው ዲዉፍ ከሴኔጋላዊ ቤተሰቦች የተገኘ ሲሆን የቻድ፣ ሴኔጋልና ፈረንሳይ ዜግነት አለው። ገና የአስራ ሰባት ዓመት ወጣት እያለ ለብቻው ወደ ፈረንሳይ ያቀናው ዲዉፍ የፖለቲካል ሳይንስ ካጠና በኋላ የፈረንሳዩ ክለብ ኦሊምፒክ ደ ማርሴል ጋዜጣ ላይ ፅሁፎችን በማበርከት ነበር ወደ ስፖርት ጋዜጠኝነት ሕይወት የገባው። ይህም በኋላ ላይ የተጫዋቾች ወኪል ሆኖ ለመስራቱ ትልቅ በር የከፈተለት አጋጣሚ እንደነበር የታሪኩ ፀሐፊዎች ይናገራሉ። ዲዉፍ የተጫዋቾች ወኪልነት ስራውን የጀመረው የቀድሞውን ፈረንሳዊ ተከላካይ ባሲል ቦሊ እንዲሁም ካሜሩናዊው ግብጠባቂ ጆሴፍ አንቶኒ ቤልን ወደ ማርሴል ክለብ በማምጣት ሲሆን በሂደት ዊሊያም ጋላስ፣ ሳሚር ናስሪና ሌሎችም እውቅ ተጫዋቾችን በደንበኝነት ይዞ ወኪል በመሆን አገልግሏል። በተለይም ኮትዲቯራዊው ኮከብ ዲዲየር ድሮግባ እኤአ ከ2003 እስከ 2004 በማርሴል ቆይታው ወቅት ወኪሉ በመሆን የተሳካ ጊዜ እንደነበረው ይጠቀሳል። ይህም በእርግር ኳስ ውስጥ የነበረው የነቃ ተሳትፎ እኤአ 2005 ላይ የማርሴል ክለብ ፕሬዚዳንት እስከ መሆን አድርሶታል። ዲዉፍ በአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች የሚሳተፍ ክለብ ፕሬዚዳንት ሲሆን በታሪክ የመጀመሪያው ጥቁር ሆኖ ይነሳል። ዲዉፍ የማርሴል ክለብ ፕሬዚዳንት ሆኖ ሲያገለግል ክለቡ በፈረንሳይ የመጀመሪያው ሊግ ሁለት ጊዜ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ ትልቅ ሚና ነበረው። እኤአ 2009 ላይም ዲዉፍ አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሾን ወደ ማርሴል በማምጣት ክለቡ የሊጉን ዋንጫ እንዲያነሳ አድርጓል። ይህም ክብር ክለቡ ከአስራ ስምንት ዓመታት በኋላ ያጣጣመው ሆኖ ተመዝግቧል። አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሾ ባለፈው የሩሲያ ዓለም ዋንጫ ፈረንሳይ ከሃያ ዓመታት በኋላ ስታሸንፍ የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ እንደነበሩ አይዘነጋም። ከዚህ ድል በኋላ ከክለቡ ፕሬዚዳንትነት የለቀቀው ዲዉፍ የፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበርን መርቷል። እኤአ 2009 ላይ በፊፋ ጠቅላላ ጉባዔ ዙሪክ ላይ ተገኝቶ በፈረንሳይ እግር ኳስ ደረጃና በአጠቃላይ እግር ኳስ ውስጥ ስላለው ዘረኝነት ያደረገው ንግግር በታሪኩ ይጠቀስለታል። ዲዉፍ በአውሮፓ እግር ኳስ ውስጥ አሳሳቢ ስለሆነው የዘረኝነት ጉዳይ ጥቁሮች ሰለባ እንዳይሆኑ በጠንካራ ቃላት በዓለም ሕዝብ ፊት ቆሞ በመሟገት ይታወቃል። በስፖርት ጋዜጠኝነት ሕይወቱም ብዙዎችን በማንቃትና ጠንካራ ስራዎችን በማቅረብ የተጨበጨበለት መሆኑን በርካቶች ይመሰክሩለታል። በዚህ ወቅት ዓለምን እያስጨነቀ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ተይዞ የነበረው ዲዉፍ በቤተሰቦቹ አገር ሴኔጋል እርዳታ እየተደረገለት የቆየ ሲሆን ለተሻለ ሕክምና ወደ ፈረንሳይ ለማቅናት በተዘጋጀበት ወቅት ሕይወቱ ማለፉ ተዘግቧል። ይህም በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ በሴኔጋል የተመዘገበ የመጀመሪያው የሞት ዜና ሆኗል። ይህንንም ተከትሎ በርካታ የእግር ኳሱ ዓለም ከዋክብቶች በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን ሃዘናቸውን እየገለፁ ይገኛሉ። ዲዉፍ ድንቅ ታሪክ የሰራለት ማርሴል ክለብ በትዊተር ገፁ ‹‹ፔፕ ሁል ጊዜም በማርሴል ልብ ውስጥ ይኖራል፣ የማርሴል የምን ጊዜም ታሪካዊ ሰው ነው›› በማለት ሃዘኑን ገልጿል። የፕሮፌሽል ተጫዋቾች ማህበር በበኩሉ ‹‹ጋዜጠኛ፣ወኪልና የቀድሞ የማርሴል ፕሬዚዳንት ፔፕ ዲዉፍ ሕይወቱን ሙሉ እግር ኳስን ሲያገለግል የኖረ ሰው ነው›› በማለት አስታውሶ ሃዘኑን ገልጿል። ፈረንሳዊው የቀድሞ የሊቨርፑል አጥቂ ጅብሪል ሲሴ ዲዉፍ የማርሴል ፕሬዚዳንት እያለ ለክለቡ ተጫውቷል።‹‹የፈረንሳይ እግር ኳስ ዛሬ ድንቅ ሰው አጥቷል›› በማለት ሲሴ የተሰማውን ሃዘን በትዊተር ገፁ አስፍሯል። ሌላኛው ፈረንሳዊ የማንቸስተር ሲቲ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ቤንጃሚን ሜንዲ በበኩሉ ‹‹ድንቅ የክለብ ፕሬዚዳንት ነው፣ ከዚያም በላይ ሁል ጊዜ ለማርሴል እሴቶች የሚጨነቅ ትልቅ ሰው ነው›› በማለት ተናግሯል። አዲስ ዘመን መጋቢት 27/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29803
[ { "passage": "ሪችማን ለአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን እንደገለጸው ድምጻዊውን ያጋጠመው የልብ ህመም ከፍተኛ መጠን ያለው መድኃኒት ከመውሰድ ጋር የተያያዘ ይሆን አይሆን እንደማያውቅ መናገሩን ቲኤምዚ ዘግቧል።\n\nዲኤምኤክስ ለዓመታት ከአደንዛዥ ዕፅ ሱሰኝነት ጋር ሲታገል የነበረ ሲሆን በተደጋጋሚ ወደ ማገገሚያ ገብቶ ነበር።\n\nበአድናቂዎቹ የሂፕ ሆፕ ታላቅ ሰው ተደርጎ የሚታየው ራፐሩ፣ ፊልሞች ላይ ከመሳተፍ በተጨማሪ ከጄይ ዚ፣ ጃ ሩል፣ ኢቭ እና ኤልኤል ኩል ጄ ጋር በጋራ የተለያዩ ሙዚቃዎችን ተጫውቷል።\n\nዲኤምኤክስ በሙያው ከ20 ዓመት በላይ የቆየ ሲሆን ክሬድል 2 እና ሮሚዮ መስት ዳይ ፊልሞች ላይ ከጄት ሊ ጋር ተውኗል።\n\nየ50 ዓመቱ ራፐር የመታወቂያ ስሙ አርል ሲመንስ ሲሆን ሆስፒታል የገባው አርብ ማታ መሆኑን ጠበቃው አክሎ ተናግሯል።\n\nበዙሪያው ቤተሰቦቹ መኖራቸውንም ገልፀዋል።\n\n\"በመተንፈሻ መሳሪያ ታግዞ ነበር የሚተነፍሰው፤ አሁን ግን እርሱ ተነቅሎ በራሱ እየተነፈሰ ነው\" ብሏል ጠበቃው።\n\nየ15 ልጆች አባት የሆነው ራፐሩ ከዚህ ቀደም የጦር መሳሪያ እና አደንዛዥ ዕፅ በመያዝ፣ በግዴለሽነት በማሽከርከርና በእንስሳት ላይ ያልተገባ ነገር በመፈጸም እስር ቤት ገብቶ ያውቃል።\n\nእንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2018 በታክስ ማጭበርበር ተከስሶ ችሎት ፊት በቀረበበት ወቅት ከሙዚቃ ሥራዎቹ መካከል አንዱን ለዳኛው በመጫወት የመገናኛ ብዙሃን ደጋግመው ስሙን ያነሱት ነበር።\n\nበወቅቱ ዳኛው ሙዚቃውን ካዳመጡ በኋላ ዲኤምኤክስ \"መልካም ሰው ነው\" በማለት የአንድ ዓመት እስር ብቻ ፈርደውበታል።\n\nበ2016 ደግሞ በኒው ዮርክ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆቴል የመኪና ማቆሚያ ስፍራ ላይ ሳለ ለመተንፈስ ተቸግሮ የህክምና እርዳታ ለማግኘት ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ነበር።\n\nጠበቃው \"አርል በጣም መልካመ ሰው ነው፤ ታሪክ መናገር የሚችል እጅግ መልካም ሰው\" በማለት በደረሰበት የጤና መታወክ የተሰማውን ሐዘን ገልጿል።\n\n ", "passage_id": "e35e9bf94d634773828915706badbd21" }, { "passage": "ስፔን ውስጥ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ የጣሊያን ብሔራዊ ቡደን ዋንጫውን ባነሳበት ጊዜ ፓውሎ ሮሲ ኮከብ ግብ አግቢና ተጫዋች በመሆን የተመረጠ ሲሆን ዝናው በዓለም ዙሪያ ናኝቶ ነበር።\n\nሮሲ በጣሊያን ሊግ ውስጥ እውቅናን ማግኘት የጀመረው ቪያቼንዛ ለተባለው ቡድን በተጫወተበት ጊዜ በርካታ ግቦችን በማስቆጠር የነበረ ሲሆን፤ ከዚያም ወደ ታዋቂዎቹ የጣሊያን ክለቦች ጁቬንቱስና ኤሲ ሚላን ተዘዋውሮ ተጫውቷል። \n\nየጣሊያን መገናኛ ብዙሃን ሮሲ ለረጅም ጊዜ በህመም ከቆየ በኋላ ሕይወቱ ማለፉን ገልጸዋል። \n\nየሮሲ ባለቤት ፌዴሪካ ካፔሌቲ ሞቱን ተከትሎ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጿ ላይ ከሮሲ ጋር አብረው የተነሱትን ፎቶ በመለጠፍ \"ለዘላለም\" የሚል ጽሁፍ አስፍራለች። \n\nባለቤቱ፤ ፓውሎ ሮሲ በምን ምክንያት ለሞት እንደበቃ ምንም ያለችው ነገር ግን የለም። \n\nሮሲ ለጣሊያን ብሔራዊ ቡድን በተጫወተባቸው 48 ጨዋታዎች ላይ 20 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ በሴሪ አ ለቪያቼንዛ፣ ፔሩጂያ፣ ለጁቬንቱስ፣ ሚላንና ቬሮና በተጫወተባት ጊዜ ከ100 በላይ ግቦችን አስቆጥሯል። \n\nበ1077 (እአአ) ወደ ሴሪ አ እንዲያድግ ያደረገው ቪያቼንዛ ቡድን የሮሲ ሞት በክለቡ ላይ የፈጠረውን ስሜት \"አንዳንድ ጊዜ ሁላችንም የተሰማንን ህመም የምንገልጽባቸው ቃላቶችን እናጣለን\" በማለት ባወጣው መግለጫ ላይ አስፍሯል። \n\nሮሲ በዓለም ዋንጫ የአገሩ ብሔራዊ ቡድን ዋንጫ እንዲያገኝ ካደረገ በኋላ በወቅቱ ለአውሮፓዊ የዓመቱ ምርጥ የእግር ኳስ ተጫዋች ይሰጥ የነበረውን የቦሎን ዶር ሽልማትን አግኝቶ ነበር። \n\nፓውሎ ሮሲ እግር ኳስ መጫወት ካቆመ በኋላ ለስካይ፣ ሚዲያሴት እና ራይ ለተባሉ የመገናኛ ብዙሃን የእግር ኳስ ተንታኝ ሆኖ ሰርቷል። \n\n ", "passage_id": "caac264224115e1ba9b2bdfe898c8ca7" }, { "passage": "በተረጋጋ አንደበት ነገሮችን የማስረዳት ችሎታውና ገለፃው ትኩረትን የመሳብ አቅም አለው፡፡ አንደበተ ርቱዕ ነው፡፡ ምናልባት የሬዲዮ ጋዜጠኛና የሥነ ፅሁፍ ባለሙያ መሆኑ ሳይጠቅመው አልቀረም፡፡ “ስለ ኢትዮጵያ ክፉ ክፉውን ሳይሆን ቀናውን ማሰብ ይበጃል” የሚል ፅኑ እምነት አለው፡፡ በእድሜም በእውቀትም መብሰሉ ያመጣው ድምዳሜ ይመስላል። መንፈሰ ጠንካራ እንደሆነ ሁለመናው ይመሰክራል፡፡ ጋዜጠኛና መምህር ደምስ በለጠ፤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት የአገሩን መሬት የረገጠው ከ32 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ በገባ በሳምንቱም በአዲስ አድማስ ቢሮ ተገኝቶ፣ ሰፊ ቃለ ምልልስ አድርጓል፡፡ የስደት ህይወቱን፣ የወደፊት ህልሙንና ራዕዩን፣ ለአገሩ ያለውን በተስፋ የተሞላ ምኞት አውግቶናል - በቃለ ምልልሱ፡፡ በሳምንቱ ድንገተኛ ህልፈቱ ተሰማ፡፡ ለብዙዎች እጅግ አስደናጋጭና አሳዛኝ ነበር፡፡ ለ7 ዓመታት ያህል በሩሲያ በትምህርትና በተለያዩ የሚዲያ ስራዎች የቆየው ጋዜጠኛ ደምስ፤ በሰሜን አሜሪካ በሬዲዮ ጋዜጠኝነትና በመምህርነት ስራ ላይ ተሰማርቶ ለ25 ዓመታት ኖሯል፡፡ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢንተርኔት የአማርኛ ሬዲዮ መስራቹ ጋዜጠኛ ደምስ፤ ወደ አገሩ የተመለሰው ባዶ እጁን አልነበረም፡፡ ብዙ ተስፋና ራዕይ ሰንቆ ነበር፡፡ በሚዲያው ኢንዱስትሪ በርካታ ተግባራትን ለማከናወን፣ በሃገሪቱ የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ ለማገዝና የህዝብ አንደበት ለመሆን እንዲሁም በኢትዮጵያ ጠንካራ ሚዲያ ለማቋቋም እቅድ እንደነበረው አውግቶናል፡፡ ለአዲስ አድማስ በቋሚነት ለመጻፍ እንደሚፈልግም  ነግሮን ነበር፡፡  አዲስ አበባ ተወልዶ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ያደገው ደምስ በለጠ፤ ከአሜሪካ ከመጣ በኋላ ከባህር ዳር በመጀመር በርካታ የኢትዮጵያ ከተሞችን የመጎብኘት ዕቅድ ነበረው፡፡ “ኢትዮጵያዊነት ፅኑ ማንነት ነው” የሚለው ደምስ፤ ላለፉት በርካታ ዓመታት በአማራ ህዝብ ላይ ሲደርስ የነበረውን ግፍና በደል፣ ስደትና መፈናቀል---ሳይታክት በሬዲዮ ፕሮግራሙ ሲያጋልጥ የቆየ ሲሆን በሃገር ቤትም  የጀመረውን ትግል በሚዲያው ለመቀጠል ዓላማ ነበረው፡፡ ከመንግስት ጋር በነበረው የፖለቲካ ልዩነት ሳቢያ ሶስት ወንድሞቹ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ወደ አገሩ መጥቶ መቅበር ባለመቻሉ በእጅጉ እንደሚያስቆጨው የነገረን ጋዜጠኛ ደምስ፤ በሌላ በኩል ፈጣሪ እድሜ ሰጥቶ ያቆየለትን ወላጅ እናቱን በ92 ዓመታቸው ለማግኘት በመቻሉ የተሰማውን ደስታ አጋርቶን ነበር። የሚያሳዝነው ይሄን ደስታውንና ናፍቆቱን በቅጡ ለመወጣትና ለማጣጣም በቂ ጊዜ ሳያገኝ ድንገት ማለፉ ነው፡፡   የዚህ ባለ ብዙ ህልም መምህርና ጋዜጠኛ ድንገተኛ ዜና እረፍት ሲሰማ ብዙዎች ተደናግጠዋል፤ ተረብሸዋል። ደምስ እንዴት ሞተ? በምን ምክንያት ሞተ? እስካሁን ምላሽ ያላገኘ ጥያቄ ነው፡፡ ፖሊስ ጉዳዩን በትኩረት መርምሮ የአሟሟቱን መንስኤ ይፋ እንዲያደርግ፣ ቤተሰቦቹ የቅርብ ወዳጆቹና የሙያ አጋሮቹ እየጠየቁ ነው፡፡ በብዙ ናፍቆት ወደ ሀገሩ የተመለሰው፣ በብዙ ተስፋ ነገን ሲያልም የነበረው፤ ነገር ግን በአጭሩ የተቀጨው ጋዜጠኛ ደምስ፤ ከአዲስ አድማስ ጋር በነበረው ቆይታ፣ የዛሬ 25 አመት ከሩስያ ቋንቋ ወደ አማርኛ የመለሰውን የአሌክሳንደር ፑሽኪንን ግጥም በቃሉ ተወጥቶት ነበር። እንዲህ  በጽሁፍ አስፍረነዋል፡፡  “አስታውሳለሁ የአንድን ቅጽበት ፊት ለፊቴ አንቺ የተደቀንሽበት እንደ አጭር ጊዜ እይታ እንደ ብሩህ ንፁህ ውበት ያለ ተስፋ በሚያሰቃይ ንዴት በግርግር በስጋት በጩኸት ለረጅም ጊዜ ለስላሳ ድምጽ ተሰማኝ እና በአይነ ህሊናዬ ውብ ድምጽሽ ታየኝ አመታት አለፉ የአውሎ ነፋስ መንፈስ ሽብርም አጠፋው የቀድሞውን ህልምእና ረሣሁት ያንቺን ድምጽ ለስላሳውን ሩቅ ሀገር በጨለማው ግባት ተዘርግተው የኔ ፀጥተኛ ቀናት ያለ አምላክ ያለ እምባ ያለ ፍቅር ያለ ህይወት በነፍሴ መነሳሳት ንቃት እንደገና ይኸው መጣሽብኝ ወዴት እንደ አጭር ጊዜ እይታ እንደ ብሩህ ንፁህ ውበት አምላክም ጥልቅ ስሜትም ህይወትም እምባም ፍቅርም እና ልቤ ይመታል በፍንደቃ ህያውነት ተሰማው እንደገና ነቃ”ደምስ የአሌክሳንደር ፑሽኪን ግጥሞችን ከሩስኪ  ወደ አማርኛ መተርጎሙን አውግቶናል፤ ነገር ግን ለህትመት አልበቁም፡፡ የራሱም በርካታ ግጥሞችም አሉት፡፡ ሥራዎቹን ለህትመት ማብቃት ቢቻል የደምስ ነፍስ ጮቤ ትረግጣለች፡፡ ልፋቱም ለፍሬ ይበቃል። ቤተሰቦቹና የቅርብ ወዳጆቹ ትኩረት ቢሰጡት መልካም ነው፡፡  “ህይወት አጋጣሚ ነች” የሚለው መምህሩና ጋዜጠኛው፤ “ሰዎች አጋጣሚያቸውን መኖር አለባቸው” ብሎ ያምናል፡፡ እርሱም አጋጣሚውን ኖሯል፡፡ ነፍሱ በሰላም ትረፍ!! የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል፣ በጋዜጠኛና መምህር ደምስ በለጠ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማውን መሪር ሃዘን እየገለፀ፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል፡፡ ", "passage_id": "dd80c3273077f67e59baa78b84e447fb" }, { "passage": "እኩለ ሌሊት አካባቢ ነው። ማኅበራዊ የብዙኀን መገናኛዎች ይልቁንም ፌስቡክ ግን እኩለ ቀን የሆነ ያህል ብዙዎች ሲመላለሱበት ነበር። ሁሉንም ያስደነገጠ፣ ያስጨነቀና ያሳዘነ ጉዳይ በዜና ተሰራጭቷል። ‹ውሸት አድርገው! ሕልም ይሁን!› ብሎ የሚጸልየውም ጥቂት አይመስልም። ዜናው በእርግጥም ልብ የሚሰብር ነበር። ድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ በጥይት መመታቱንና ጳውሎስ ሆስፒታል ቢገባም ሕይወቱን ማትረፍ እንዳልተቻለ ነው።ይህን ጉዳይ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠቅሶ እውነት እንደሆነ አረጋገጠ። ከዛች ቅጽበት ጀምሮ የነበረው ሁሉ እንዳልነበር ሆነ። የአዲስ አበባ ብሎም የመላው አገሪቱ ሰላም ተናጋ። የወጣቱ ድምጻዊ ኅልፈት ሐዘን የተሰማቸው ሰዎች ሐዘናቸውን የሚያስተናግዱበት ፋታ አላገኙም። ሞቱን ምክንያት ያደረጉ አለመረጋጋቶች ተከተሉ።ወደ አዲስ አበባ መግቢያ የሆኑ የተለያዩ አቅጣጫዎች ቁጣና ሐዘንን በተመሉ ወጣቶች ተጥለቀለቀ። በሌሊቱ ከሰባት ሰዓት ጀምሮም ወጣቶች በብዛት አዲስ አበባ ተገኙ። በርካታ የኦሮሚያ ክልል ከተሞችና አዲስ አበባም ጭምር ታወኩ። ‹ሀጫሉን ማን ገደለው፣ ለምን ተገደለ› በሰዓቱ ለዚህ መልስ የሚሰጥ አልነበረም። በማግስቱ ከረፋድ ጀምሮ ለጸብ አጫሪነት የተሰማሩ የሚመስሉ መገናኛ ብዙኀን ‹እነ እገሌ ናቸው የገደሉት› አሉ።ይህን ተከትሎ ብጥብጥና አለመረጋጋት ባሰ። በአዲስ አበባ የተለያዩ ቤቶች በድንጋይ ናዳ መስታወቶቻቸው ሲረግፍ፣ በየስፍራው ንብረት በእሳት ወደመ። ብዙዎቹ ዘነጉ፣ ስለእነርሱ ፍትህ ማግኘትና ነጻነት ባመነበት መልኩ ሲታገልላቸው የነበረውን ሰው፣ የፖለቲካቸው መጠቀሚያ አደረጉት። በሞቱ እንደመዘባበት ባለ መልኩ ተቀባበሉት። ሰላም በአንድ ጊዜ ሸሸች። ‹ጂራ ጂራ ጂራ!› ሲል ያቀነቀነው ድምጻዊ፣ የ36 ዓመቱ ሀጫሉ ሁንዴሳ ወደማይመለሱበት ሄደ።\nሀጫሉ ትውልድና እድገቱ በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ከተማ ነው። በ1976 ይህቺን ዓለም የተቀላቀለው ሀጫሉ በ1981 ትምህርት ጀምሮ አንደኛ ደረጃ እንዲሁም ኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአምቦ የመጀመሪያና ኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተምሯል። ከምንም በላይ ታድያ ከእጁ ክራር ተነጥሎ እንደማያውቅ በሕይወት ታሪኩ ላይ ከቤተሰቦቹና ጓደኞቹ እማኝነት ተጠቅሶ ሰፍሯል።\nወላጅ እናቱ ጉዲቱ ሆራ እና አባቱ ሁንዴሳ ቦንሳ ከወለዷቸው ዐስር ልጆ መካከል ሀጫሉ አምስተኛ ልጃቸው ነው። ከእርሱ ጋር ስድስት ወንድ ልጆችን እና አራት ሴቶችን ወልደዋል። ልጃቸው ሀጫሉ ታድያ ገና በለጋነት ነበር ፖለቲካው ትኩሳትና ግለት፣ ተቆርቋነትም ተሰምቶት የቀረበውን ትግል የተቀላቀለው።ይህም በሕይወቱ ቀላል የማይባልን መስዋዕትነት እንዳስከፈለው ዛሬ ካለፈ በኋላ ብዙዎች ተረድተዋል። በተለይም የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪ ሳለ በተቀላቀለው ትግል የተነሳ እርሱና ሌሎች ጓደኞቹ ለእስር ተዳርገዋል። ይህም በ1995 የሆነ ሲሆን፣ ሀጫሉ አምቦ በሚገኝ እስር ቤት አምስት ዓመታትን አሳልፏል። ይህ ከእድሜው፣ ከሕይወቱ፣ ከትምህርቱ፣ ከነጻነቱ የተነጠቀውን አምስት ዓመት በማረሚያ ቤት እንዲሁ ያሳለፈው አልነበረም።እንዲህ ነው፤ ይልቁንም በእስር ቤቱ ትምህርት እንዲጀመር ከማረሚያ ቤቱ አመራር ጋር ተነጋገረ። ያንንም ሊያሳካ ቻለ። አልፎም ለጥሞና የረዳው ይመስላል፣ ከእስር ከተፈጣ ስድስትና ሰባት ወር ገደማ ቆይቶ ያወጣው የመጀመሪያ አልበሙ ‹ሰኚ ሞቲ› የግጥምና የዜና ሥራዎችን በዛው በእስር ሳለ ነው ያሰናዳቸውና በሐሳቡ የጨረሰው።ሀጫሉ አዲስ አበባ እንደመጣ ከታምራት ከበደ ጋር ተገናኝቶ በእስር ቤት ሳለ የወጠነውን የመጀመሪያ አልበሙን በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ አጠናቀቀና ለአድማጭ አደረሰ። ይህ አልበሙ ነበር ከአድማጩና ከሕዝብ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተዋወቀው። ይሄኔ ሀጫሉ የአምቦ ልጅ ብቻ እንዳይደለ ታወቀ፣ የአገር ልጅ ነውና፣ የኢትዮጵያ።ከአልበሙ ውስጥ ሰኚ ሞቱ የተሰኘው ሙዚቃ የሙዚቃ ቪድዮ ተሠራለት። ቀጠን ያለ፣ ከገጹ ፈገግታ የማይጠፋና በአፋን ኦሮሞ የሚያንጎራጉረውን ሙዚቃ ቋንቋውን መረዳት ለማይችሉ ቅንጥስጥስ እያለ በእንቅስቃሴው የሚተርክ ዓይነት ሙዚቀኛ ነው። በተለይም ‹ሰኚ ሞቲ› የተሰኘው ሙዚቃ ቪዲዮ ተሠርቶለት ለእይታ ከቀረበ በኋላ ሀጫሉ ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለዐይንም እንግድነቱ አበቃ።\nሀጫሉ ጽናቱን ያሳየበትን አንድ ድርጊት የፈጸመው ከዚህ በኋላ ነው። አቋርጦ የነበረውን ትምህርት ቀጠለና አጠናቀቀ። በሙዚቃ ሥራውም ከእለት እለት እያደገ ከጃምቦ ጆቴ ጋር ስብስብ ሥራዎች አሳተሙ። ሕልሙም ከዚህ ጋር የሚያያዝ ነበር፣ በተለይም ከጃምቦ ጆቴና ሌሎች ድምጻውያን ጋር በመላው ኦሮሚያ የሙዚቃ ድግስ ወይም ኮንሰርት የማቅረብ ፍላጎት ነበረው።ሕይወት ለዚህ ወጣት የሙዚቃ አፍቃሪና ላመነበት ሐሳብ ተሟጋች የሆነ ሰው ተረጋግታ አልሄደችም። አንድ የሙዚቃ ሥራ ለማቅረብ በጉዞ ላይ ሳለ የመኪና አደጋ አጋጠመው። ለሞት ግን አልዳረገውም፣ ሆኖም በደረሰበት ጉዳትና ከዛ በማገገም በወሰደበት ጊዜ ለበርካታ ዓመታት ከሙያው እንዲርቅ ግድ አለው። አልተሸነፈም፣ ደግሞ ተነሳ። ‹ዋኤ ኬኛ› የተሰኘ ኹለተኛ አልበሙን ሠራ። ከዚህ በኋላ አሜሪካ ሄደ። በአሜሪካ የመጀመሪያ ኮንሰርቱን አቀረበ። ጥሪ በተደረገለት ሁሉ በአረብና መካከለኛው ምሥራቅ አገራት ሙዚቃውን አቅርቧል። ባቀረበበትም ከፍተኛ ተቀባይነት ከማግኘቱም በላይ፣ ‹እዚህ ቆይ! አትሂድ› ያሉት አልጠፉም። እርሱ ግን ለሙያው ፍቅርና ለቤተሰቡ ክብር፣ ወገኑና አገሩም ማገልገልን መርጦ አገሩ ተመልሷል።‹ማላን ጅራ› የተሰኘ ሙዚቃው አሁን ላይ ብዙዎች ደጋግመው የሚሰሙትና ቋንቋውን የማይረዱ ሳይቀሩ አብረው የሚወዘወዙበት ድንቅ የሙዚቃ ሥራው ነው። የጥበብ ሰዎችና ሙዚቀኞች ለሰብአዊ ድጋፍና ኅብረት ባስፈለገበት ጊዜ አቤት ለማለት ፈጣን፣ አጋዥና ምን እንታዘዝ ባይ ናቸው። የፖለቲካው ነገር አልጥም ሲላቸው፣ ነገሮችን መቃወም ሲፈልጉና ድምጻቸውን ማሰማት ሲሹ ፍጥነታቸው በዛ ልክ አይደለም። ጥቂቶች ግን በስንኞች ይቀኛሉ፣ ሕዝቡም መፍትሄ እንዳገኘ ሁሉ አብሮ ያዜማል።ሀጫሉ እንዲህ ካሉት ሙዚቀኞች መካከል ነው። በዚህ ዘርፍ እንዲደነቅ ያደረገውም የሚያምንበትን በድፍረት ስለሚናገርና ዝም በተባለበት፣ ወይም ሐሳብና ጭኝቀትን ሰው በለሆሳስ በሚነጋገርበት ጊዜ እንኳ እርሱ ድምጽ ማጉያውን አንስቶ፣ ግጥሞቹን ከዜማ አጣምሮ ስለፍትህ የሚዘምር መሆኑ ነው።‹ማላን ጂራ› የሚለውን ሙዚቃውን በድምጽ ብቻ ሳይሆን በምስል ሲያቀርብ፣ የሙዚቃውን ጭብጥ ቋንቋውን የማይረዳ እንኳ በቀላሉ እንዲገባው አስቻለ። መለያየት፣ በትውልድና በነገ ውስጥ የሚገኝ ተስፋ፣ እምነትና ጽናትን በዚህ የሙዚቃ ስንኝ ቀለምነት በብዙ ሰው አእምሮ ሸራ ላይ ሳለ። ጥበብ ስለራሷ ብቻ ሳይሆን፣ ለማኅበረሰብ ልትሰጥ በምትችለው አገልግሎት ውስጥ ልትታይ ቻለች።‹ማላን ጂራ› የወጣው በ2007 ነው፣ ከአምስት ዓመት ገደማ በፊት። ይህም የኦሮሞ ወጣቶች ጥያቄ ጎልቶ የተነሳበት ወቅት ነው። እርሱም ቢሆን ሙዚቃውን የሠራው በወቅቱ የነበረው ሙቀት መነሻ ሆኖት እንደሆነ መናገሩን የተለያዩ መገናኛ ብዙኀን አብሮን አደረገው ካሉት ቆይታ ጠቅሰው ገልጸዋል።‹ማላን ጅራ› ምኑን አለሁት እንደማለት ነው። በኋላ ታድያ ይህን ሙዚቃ ተከትሎ በሠራቸው ሥራዎች የፖለቲካውን ሂደትም አብሮ የሚተርክ ይመስላል። ይልቁንም በ2010 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን መምጣታቸውን ተከትሎ፣ የተመኙት ለውጥ ሲመጣ፣ ‹ጂራ ጂራ!› ወይም ‹አለን አለን!› የተሰኘ ሙዚቃን ሠራ።\nካፒታል ሆቴል የተካሄደን አንድ መድረክ ጥቂት የማይባሉ መገናኛ ብዙኀን ከ‹አንድ አፍታ› ዩትዩብ ቻናል ተውሰው ሲያጋሩት ነበር። በዛም ላይ ድምጻዊው ድምጽ ማጉያውን ጨበጠና ወደ መድረኩ ወጣ። ያደረገው ንግግር ሐሳቡ ሲጨመቅ፣ ቃል በቃል ሳይሆን ሙሉ በሙሉ በተቀየረ አገላለጽ፣ እንዲህ የሚል ነበር፣ ‹ከያኒያን ሩኅሩህ ናቸው። ለአድማጭ፣ ተደራሲ፣ አንባቢ፣ ተመልካች ወዘተ ያላቸውን ከመስጠት አይቆጠቡም። በማኅበራዊ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በፖለቲካውም ጭምር የሕዝብን ድምጽ ማሰማት ተገቢ ነው። እንደ ርኅራሄና እንደ ልገሳም የሚቆጠር ነው።›\nያንን እርሱ አድርጓል። ያመነበትን ከመናገር ወደኋላ የማይለው ሀጫሉ፣ በተለያዩ የመድረክ ሥራዎቹም በሽለላና በፉከራ መልክ የሚያቀርባቸው የተቋጠሩ ስንኞች፣ አስደንግጦ ‹ኧረ ጸብ እንዳያመጣ!› የሚያሰኛቸው እንዳሉ ሁሉ፣ አብረውት በቁጭት ሲያቀንቅኑ የሚታዩ ጥቂት አይደሉም።ካለው ላይ በማካፈልና በመስጠት የሚወደሰው ሀጫሉ፣ የኦሮሞ ተወላጆች ከሶማሌ በተፈናቀሉ ጊዜ ድጋፍና ገቢ ማሰባሰብ ላይ እንዲያግዝ ጥሪ ሲቀርብለት፣ አቤት ወዴት ከማለት ውጪ ደጅ አላስጠናም፣ አላንገራገረም። ሌሎችንም ቀስቅሷል። በ2011 የአድዋ ድል በዓልን በሚመለከት በቀረበ ዝግጅት፣ የኦሮሞ ተዋጊዎች በጦርነት የነበራቸውን ከፍ ያለ ሚና አንስቷል። ለአምቦ የከተማ ልማት ሥራ ካለው ገንዘብ ከመስጠት አልቦዘነም።\nለጥፋት የተሰማሩ እጆች ክፍተትንና አጋጣሚን ይጠቀማሉ። ካልተገኘ ደግሞ ይፈጥራሉ። ሀጫሉ በሕይወት በነበረበት ዓመታት በሐሳቡ የማይስማሙና የሚቃወሙት ጥቂት አይደሉም። የሚደግፉትም እንደዛው በርካታ ናቸው። እርሱም ያመነበትን ከመግለጽ ወደኋላ አይልም፣ አላለም ነበር። በተለይም በታሪክ ዙሪያ በሚነሱ አለመግባባቶች ውስጥ፣ የሚያምንበትን ይገልጻል።\nሰው በዙሪያው ያለ እንቅስቃሴ ውጤት እንደሆነው ሁሉ፣ ገና በልጅነት እድሜ በእስር ያሳለፈው ሕይወት፣ በማኅበረሰቡ ውስጥ የሚንሸራሸሩ ሐሳቦች፣ እድሜው፣ እርሱ ከተገኘበት ሐሳብ በተቃራኒ አቅጣጨ የሚመጡ ወቀሳዎች፣ በመጨረሻም የራሱ ግንዛቤና እይታ ሀጫሉን ሠርተውታል። ወጣት ነበር፣ ራስን በመፈለግ የሰው ልጅ የኑሮ ዑደት ውስጥ እየጎተቱ ጊዜውን የበሉበት ኹነቶች ቢቀናነሱ፣ የኖረው ጥቂቱን ነው።ይህ ሁሉንም ያሳዘነ ክስተት ነው። ጉዳዩም የሐሳብ ልዩነት አይደለም፣ እውነትና ፍትህ፣ ሰው የመሆን ጉዳይ ነው። ‹‹ኤሰ ጅራ› የተሰኘ ነጠላ ዜማ እየሠራ የነበረው ሀጫሉ፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነው። ወላጅ አባቱ የቀብር ስነስርዓቱ ሊፈጸም በአምቦ ስታድየም በተከናወነ የሽኝት ሥነ ስርዓት ላይ አሉ፣ ‹የልጄ ደም በከንቱ ፈስሶ እንዳይቀር ወደ ፈጣሪ ለምኑልኝ!› በሞቱ እናተርፋለን ያሉ ሁሉ እንዳይሆንላቸው ከሕግና ፍትህ ሁሉም እውነቱን ይጠበቃል።አዲስ ማለዳ ለድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ ቤተሰቡ፣ አድናቂና ወዳጆቹ ሁሉ መጽናናትን እንዲሁም ለነፍሱ ዘለዓለማዊ እረፍትን ትመኛለች።ቅጽ 2 ቁጥር 87 ሠኔ 27 2012", "passage_id": "4a4c38b71aa7e33162b6bfa6bf06e3ba" }, { "passage": "አንደኛው በደቡም ምሥራቅ አውሮጳ የሚገኙ ቴኒስ ተጫዋቾች ከውድድር ርቀው ስለነበር ለቀጣይ ውድድር እንዲዘጋጁ ለማድረግ ሲሆን ሁለተኛው የሚገኘው ገቢ ከኮሮና ጋር በተያያዘ የሚውል ለበጎ አድራጎት እንዲሰጥ ነበር፡፡\n\nይህ ውድድር ገና ከመጀመሩ ታዲያ አሳዛኝ ዜና አጋጥሞታል፡፡\n\nቢያንስ አራት የሚሆኑ ዕውቅ የቴኒስ ተጫዋቾች በኮሮና መያዛቸው ታውቋል፡፡ ከነዚህም መሐል ክሮሺያዊው ቦርና ኮሪክ እና ሰርቢያዊው ቪክተር ትሮይኪ እንዲሁም ቡልጋሪያዊው ግሪጎር ዲሚትሮቭ ይገኙበታል።\n\n• ኢትዮጵያ መሰረታቸውን ግብጽ ባደረጉ ቡድኖች የመረጃ መረብ ጥቃት ተሞከረብኝ አለች \n\n• የናይጄሪያ ፖሊስ በሩዝ ፋብሪካ ተቆልፎባቸው እንዲሰሩ የተገደዱ 300 ሰራተኞችን ነፃ ማውጣቱን ገለፀ\n\n• በአፍሪካ የመጀመሪያው የኮሮናቫይረስ ክትባት ሙከራ ሊደረግ ነው \n\n‹‹ይህንን የቴኒስ ውድድር ያሰናዳሁት ከቅን ልቦና ተነስቼ ነበር፡፡ ሁሉንም የጤና መመርያዎች ለመከተል ሞክረናል፡፡ ይህ አሳዛኝ ዜና በመምጣቱ ከልብ አዝናለሁ›› ብሏል ቾኮቪች፡፡\n\nየእንግሊዙ እውቅ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች አንዲ ሙሬይ በበኩሉ ‹‹ይህ ለኛ ትልቅ ትምህርት ነው›› ሲል ትዊተር ሰሌዳው ጽፏል፡፡\n\nይህንን ውድድር በዚህ ወቅት ማሰናዳት አደጋ ሊኖረው ይችላል የሚል ሐሳብ ቀድሞውንም ሲንጸባረቅ ነበር፡፡\n\nየቴኒስ ውድድሩ በጆኮቪች ሐሳብ አመንጪነት ሲሰናዳ እውቅ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋቾች ራሳቸውን ከውድድር በማራቃቸው እንደ ማነቃቂያ ሊሆናቸው ይችላል፤ በዚያውም የበጎ አድራጎት ሥራ ይሆናል በሚል ነበር፡፡\n\nጆኮቪች በድረገጹ እንደጻፈው መጀመርያ ቤልግሬድ እንደደረሰ በኮሮና መያዙ ይፋ የተደረገው ኖቫክና ቤተሰቡ ነበር፡፡ ሆኖም ምንም ምልክት አያሳይም ነበር፡፡\n\nይህ በሰርቢያ የተሰናዳው ውድድር 4ሺህ ሰዎች ታድመውታል፡፡ ሜዳ ቴኒስ ተጫዋቾችም ከውድድር በኋላ መሸታ ቤት ሲደንሱ የሚያሳይ ፎቶ ወጥቷል፡፡\n\nበመጀመርያው ቀን ውድድር የቡልጋሪያው ዲሚትሮቭ ከክሮሺያው ኮሪክ ጋር ቅዳሜ እለት ተጫውተው ነበር፡፡\n\nጆኮቪች ከዚህ ቀደም የኮሮናቫይረስ ክትባት ቢኖር እንኳ ክትባቱን ለመወጋት ፍቃደኛ እንደማይሆን በትዊተር ገጹ በመጻፉ የሴራ ንድፈሐሳብ አራማጆች ክትባቱ በቢልጌትስ የተቀነባበረ ስለመሆኑ እንደ አንድ ማስረጃ የርሱን ጽሑፍ ሲያጋሩ ነበር፡፡\n\nሚስቱ ጄሌና ከዚህ ቀደም ኮሮናቫይረስ የመጣው በ5ጂ ቴክኖሎጂ ነው የሚል ይዘት ያለው ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ ማጋራቷ ሲታይ ቤተሰቡ በወረርሽኙ ምንነት ላይ ጥርጣሬ እንደነበረው እንዲገመት በር ከፍቷል።\n\n ", "passage_id": "d4985eb127c590458d9176170cb2a342" } ]
9252ec3417bd6ce4edef640bdd44aaef
a6817872051fa117ab913c4d9ad9c3f2
ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከወዲሁ ፈተናዎችን መጋፈጥ ጀምሯል
ኦ ሊምፒክ ከጤና ስጋት ጋር የተያያዘ ባይሆንም በተለያዩ ጊዜዎች የመሰረዝና የቦታ ለውጥ ሲደረግበት ታይቷል፡፡ እኤአ የ1916 የበጋ ኦሊምፒክ በጀርመን በርሊን ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት በአንደኛ የዓለም ጦርነት ሳቢያ ተሰርዟል:: በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅትም የ1940 የክረምት ኦሊምፒክና የ1944 የበጋ ኦሊምፒክ ውድድሮች የመሰረዝ እድል ገጥሟቸዋል:: እኤአ የ1976 የክረምት ኦሊምፒክም በዴንቨር ኮሎራዶ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የኮሎራዶ ግዛት ሕዝብ ለውድድሩ የሚወጣውን ወጪ በመቃወሙ ውድድሩ የቦታ ለውጥ ተደርጎበት በአውስትራሊያ ኢንስብረክ ለመካሄድ ተገዷል፡፡ ዩ ኤስ ኤ ቱዴይ በወቅቱ እንደዘገበው የኮሎራዶው ኦሊምፒክ የቦታ ለውጥ እንዲደረግበት ውሳኔ ላይ የተደረሰው ውድድሩ ከመካሄዱ ከሦስት ዓመታት አስቀድሞ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ኦሊምፒክ በታሪክ ተራዝሞ የሚያውቅበት አጋጣሚ አልነበረም:: ዓለም በአሁኑ ወቅት እየተሸበረችበት በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ግን የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለአሥራ ስድስት ወራት ሲራዘም በታሪከ የመጀመሪያው ለመሆን በቅቷል፡፡ ይህም ለዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴና ለውድድሩ አዘጋጆች አዲስ ተሞክሮ ብቻ ሳይሆን አዲስ ፈተና ይዞ መምጣቱ አልቀረም፡፡ ይህን አዲስ ፈተናም ለመጋፈጥና ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮችን ከወዲሁ ለማስተካከል ዓለም አቀፍ ኮሚቴውና አዘጋጆቹ ከወዲሁ ሌት ከቀን እየሰሩ እንደሚገኙ ሰሞኑን ገልፀዋል፡፡ የኦሊምፒክ ስፖርቶች ዳይሬክተሩ ክሪስቶፍ ዱቢ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ‹‹ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ውስብስብ ብቻ ሳይሆን አዲስ ፈተና ገጥሞናል›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከጃፓን መንግሥት ጋር በመሆን ይህን ፈተና ለመወጣትና አሁን ዝግጁ የሆኑ ነገሮችን ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ተግባራዊ እንዲሆኑ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ ይህም ማለት ኦሊምፒኩ ከመራዘሙ አስቀድሞ በተያዘለት ጊዜ እንዲካሄድ ዝግጁ የነበሩ የኦሊምፒክ መንደሮችን፣አርባ አንድ ዋነኛየውድድር ቦታዎች፣ ከአርባ ሺ በላይ የሆቴል ክፍሎች፣ከሁለት ሺ በላይ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶችን እንዲሁም አገልግሎትና በሺዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ ቁሶችን ለማቅረብ የተደረጉ ውሎችን መልክ ማስያዝና ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ተግባራዊ የሚሆኑበትን አቅጣጫ የማስቀመጥና መልክ የማስያዝ ሥራዎች ከወዲሁ እየተሰሩ ነው፡፡ ይሁን እንጂ የዓለምን እንቅስቃሴ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሽባ ያደረገው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ነገሮችን መልክ ለማስያዝ በሚያደርገው እንቅስቃሴ አሁንም ፈተና እየሆነ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ አልሸሸጉም፡፡ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከተጠቀሱት ፈተናዎች በተጨማሪ ሌሎችም እንቅፋቶች ይኖሩበታል:: ከውድድር ጋር በተያያዘ ለኦሊምፒኩ አስፈላጊውን መስፈርት (ሚኒማ) በተለያዩ ስፖርቶች አሟልተው የነበሩ በሺ የሚቆጠሩ አትሌቶች መስፈርታቸው ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ለሚካሄደው ኦሊምፒክ ይስራ አይስራ እርግጠኞች አይደሉም፡፡ በኦሊምፒክ ለመሳተፍ በየትኛውም ስፖርት አንድ አትሌት መስፈርቶችን ማሟላት የግድ ይለዋል፡፡ ከአስራ ስድስት ወር በፊት መስፈርት ያሟላ አትሌት ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ያሟላል ወይም አሁን ያለውን አቋም ይዞ ይቆያል ማለት አይቻልም፡፡ የተራዘመው ኦሊምፒክ ሲቃረብ አትሌቶች ዳግም መስፈርት አሟልተው ይወዳደሩ ማለት ደግሞ ሌላ ጣጣ ይዞ ይመጣል፡፡ ዛሬ መስፈርቱን ያሟላ አትሌት ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ ዳግም ላያሟላ ይችላል፡፡ ስለዚህ ይህን ጉዳይ ለማስተካከል ራሱን የቻለ ትልቅ የቤት ሥራ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ይሁን እንጂ የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ኃላፊው ኪት ማክኮኔል አሁን መስፈርቱን ያሟሉ አትሌቶች ከአስራ ስድስት ወራት በኋላ መስፈርታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ይቆያል ብለዋል፡፡ ይህ በራሱ ግን ኋላ ላይ ጭቅጭቅ አለማስነሳቱን እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡ ከሰላሳ ሦስት ዓለም አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖች ከአስራ አንድ ሺ በላይ አትሌቶች መስፈርቱን አሟልተው ለውድድር እየተዘጋጁ ባሉበት ሁኔታ ኦሊምፒኩ መራዘሙ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን በኦሊምፒክ እግር ኳስ ውድድር የሚሳተፉ የወንድ ተጫዋቾች እድሜ ከሃያ ሦስት እስከ ሃያ አራት መሆን እንዳለበት ይታወቃል፡፡አሁን ኦሊምፒኩ በመራዘሙ በርካታ ተጫዋቾች ከዚህ እድሜ ሊያልፉ መቻላቸው ሌላው ፈተና ይሆናል፡፡ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴም ይህን ጉዳይ መልክ ለማስያዝ ጉዳዩ ከሚመለከተው ፊፋ ጋር በቅርቡ ውይይት ለማድረግ እንዳሰበ ተጠቁሟል፡፡ ኦሊምፒኩን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ለማስተላለፍ የተዋዋለው የአሜሪካን ኩባንያ ኦሊምፒኩ በሚካሄድበት ወቅት ከምንም በላይ የሚጠብቀው የኤንቢኤና ሌሎች ታላላቅ የአሜሪካን ቅርጫት ኳስ ውድድሮች ስለሚኖሩበት የፍላጎትና የጥቅም ግጭቶች ሊፈጠር ይችላል፡፡ ይህ ደግሞ አንዱን ወገን በቢሊዮን ዶላሮች ኪሳራ ላይ ሊጥል ስለሚችል ከባድ ፈተና እንደሚሆን ይታመናል:: በተመሳሳይ ከዚህ ዓመት የተላለፉ በርካቶቹ ዓለም አቀፍ ውድድሮች የሚካሄዱበት መሆኑ ሌላ ጣጣ ይዞ መምጣቱ አይቀሬ ነው፡፡ በነዚህ ወራት ከሚካሄዱ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮች መካከል የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናና የዓለም ውሃ ዋና ቻምፒዮና ዋነኞቹ ቢሆኑም ውድድራቸውን ለመሰረዝ ፍቃደኛነታቸውን መግለፃቸው ይታወቃል፡፡ ይህ አበረታችና ለዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ተስፋ የሰጠ ቢሆንም በነዚህ አካላት መካከል ተጨማሪ የውል ስምምነት እንደሚኖር ይጠበቃል፡፡ ይህ ምናልባትም ሌሎቹ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖችም ለኦሊምፒክ ቅድሚያ እንዲሰጡ ማነሳሳት ቢችልም ወቅቱ በጣም ከፍተኛ ሙቀት የሚኖርበት መሆኑ ለውድድሮች አስቸጋሪ እንደሚሆን ስጋት አሳድሯል:: ምንም ይሁን ምንም ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ የጃፓን መንግሥትን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ እንደሚገቡ ቀደም ሲል ተዘግቧል፡፡ የጃፓኑ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም ገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ ኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል ተናግሯል፡፡ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለዚህ ኪሳራ ስጋት ሰላሳ ሦስቱንም ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን የገባ ቢሆንም በቂ እንደማይሆን ታምኖበታል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ቶማስ ባኽም ኦሊምፒኩ መራዘሙን በገለፁበት ወቅት ከባድ ኪሳራ እንደሚኖር በማመን ሁሉም ባለድርሻ አካላት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል:: ከባዱን መስዋዕትነት ማን እንደሚከፍልና ጫናው በየትኛው ወገን ትከሻ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ግን ዛሬ ላይ ቆሞ በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 28/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29896
[ { "passage": "የዓለምን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ወደተለየ አቅጣጫ ያዞረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በስፖርቱ ዓለም ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተዘርዝሮ የሚልቅ አይደለም። አንዳች ውድድር በዓለም ላይ እንዳይኖር ከማስገደድ ባለፈ የስፖርቱን ዓለም ሽባ አድርጎታል። ብዙ ታቅዶባቸው፣ብዙም ተለፍቶባቸው ለዓመታት በዝግጅት ላይ የነበሩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በትልቅ ኪሳራ የሚካሄዱበት ጊዜ እንዲራዘም ግድ ብላል። \nየኮሮና ቫይረስ ስርጭት በዓለም ዙሪያ ከተንሰራፋ ወዲህ በግለሰብ ደረጃ ካልሆነ በስተቀር የትኛውም የስፖርት እንቅስቃሴ ተገድቦ እንደቆየ ይታወቃል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ይመለሳሉ የሚል ተስፋ የለም። ይሁን እንጂ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሐግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር እንደሚመለሱ ተስፋ መስጠታቸው አልቀረም። የዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን ለግሰዋል። \nበዓለማችን ብሎም በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ስርጭትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የስፖርት ቤተሰቡ መደበኛ እንቅስቃሴውን ገቶ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ ከጀመረ ሰነባብቷ። የስፖርት ቤተሰቡ ወረርሽኙን ለመከላከል ግንዛቤ ከመፍጠር እስከ ደም ልገሳ፤ ከቁሳቁስ እስከ ገንዘብ ድጋፍ በማድረግ አጋርነቱን አሳይቷል ፤ በማሳየት ላይም ይገኛል። \nወረርሽኙ በዓለም ላይ ከተከሰተና ከተስፋፋ ወዲህ የስፖርቱን ዘርፍ ክፉኛ የጎዳው ሲሆን የአገራችንን ጨምሮ በዓለም ላይ በርካታ ታላላቅ ውድድሮች እንዲቆሙ አስገድዷቸዋል። በተለይም ወረርሽኙን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በተወሰዱ እርምጃዎች ስልጠናዎች፣ ውድድሮች ቁመዋል ፤ ስፖርተኛው እና የስፖርት ቤተሰቡ ከፍተኛ የሆነ የስነ ልቦና እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አጋጥሟቸዋል ። \nበርካታ የስፖርት ክለቦች የመፍረስ አዳጋ ተደቅኖባ ቸዋል፤ አንዳንዶቹም ለስፖርተኞች ወርሃዊ ደመወዝ እስከ መከልከል ደርሰዋል። በመሆኑም የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በወረርሽኙ ወቅት እና ከወረርሽኙ በኋላ ስፖርቱ እንዴት ወደ ነበረበት መመለስ ያስችላል የሚለውን የሚያጠና እና ለመንግሥት የሚያቀርብ ጠንካራ ኮሚቴ መቋቋሙን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጅሎ መናገራቸውን የተቋሙ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ ላይ ተዘግቧል። \nየተቋቋመው ኮሚቴ አብይ እና ቴክኒካል ኮሚቴ ያለው ሲሆን አብይ ኮሚቴው በባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ጣሰው የሚመራ ይሆና። ቴክኒካል ኮሚቴው ደግሞ በአቶ ዱቤ ጅሎ እንደሚመራ ታውቋል። \nኮሚቴው አጠቃላይ የኮሮና ወረርሽኝ በአገራችን ስፖርት ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና እና መፍትሔዎችን በማጥናት ሰነዱን ለመንግሥት የሚያቀርብ ይሆናል። በጥናቱም የሌሎች አገራት ተሞክሮ ምን እንደሚመስል ተካቶ እንደሚቀርብ አቶ ዱቤ አብራርተዋል። \nጥናቱን መሠረት በማድረግ መንግሥት ስፖርቱ ለአገራችን ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ ግምት ውስጥ በማስገባት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምክትል ኮሚሽነሩ ገልፀዋል ።አዲስ ዘመን ግንቦት 27/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "24c212eb0cbc2bfc4fa9a396312bd847" }, { "passage": "\nአለምአቀፉ የኦሎምፒክ ኮሚቴ ከትናንት ጀምሮ እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ስብሰባ የቶኪዮ 2020 የኦሎምፒክ ውድድርን ለሌላ ጊዜ ማስተላለፍን ጨምሮ ሌሎች አማራጮችን እያየ ይገኛል፡፡\nኮሚቴው የተሰበሰበው እየተስፋፋ የመጣው ኮሮና ቫይረስ በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ላይ ጥላ መጣሉን ተከትሎ ነው፡፡ ኮሚቴው ኮሮና ቫይረስ ሁለት አማራጮችን እንዲያስቀምጥ እንዳስገደደው አስታውቋል፡፡\nኦሎምፒኩ የሚጀመርበትን ሐምሌ 17ን ወደ ኋላ መጎተት ወይንም ወድድሩን በአንድ አመት ወይንም ከዚያ በላይ ወደፊት መግፋት ሲሆን መሰረዝ ግን ችግሩን እንደማይፈታና ማንንም እንደማይጠቅም ኮሚቴው አስታውቋል፡፡ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ “ስለዚህ መሰረዝ አጀንዳ አይደለም”፤ ዝርዝር ውይይቶች በሚቀጥሉት አራት ሳምንታት ይካሄዳሉ ብሏል፡፡\nየኮሚቴው ኦሎምፒኩን ለማስተላለፍ ማሰቡ በአለም አትሌቲክስ፣በአለምአቀፍ ፓራኦሎምፒክ ኮሚቴና በትላልቆቹ ብሄራዊ የኦሎምፒክ ኮሚቴዎች በበጎ ተወስዷል፡፡\nኮሚቴው በከፊልም ቢሆን ሀሳቡን ለመቀየር የወሰነው፣ ከአትሌቶች፣ከፌደሬሽኖችና ከብሄራዊ ኮሚቴዎች የመጣውን ጫና ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የቶኪዮ ኦሎምፒክ አዘጋጆች ግን ወድድሩ በተያዘለት ጊዜ እንዲካሄድ እየወተወቱ ይገኛሉ፡፡\n\n\n", "passage_id": "dd9ba197cb508034d684b1fe8606cd94" }, { "passage": "የዓለም አትሌቲክስ ከዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ምክንያት ከውድድር በመራቃቸው የገንዘብ ችግር ሊገጥማቸው ይችላል ለተባሉ አትሌቶች ድጋፍ እንደሚያደርግ ባለፈው ሚያዝያ መጨረሻ ማሳወቁ ይታወሳል። የዓለም አትሌቲክስ ለዚሁ ድጋፍ እንዲውል አምስት መቶ ሺህ ዶላር ማዘጋጀቱ የሚታወቅ ሲሆን ይህን ድጋፍ ለአትሌቶች ለማድረስ የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንቱ ሴባስቲያን ኮ በሊቀመንበርነት የሚመሩት የባለሙያዎች ቡድን ተቋቋሞ በስድስት ዞኖች በተከፋፈለው የዓለም አትሌቲክስ አባል አገራት የሚገኙ አትሌቶች የሚያቀርቡት የድጋፍ ጥያቄ ተጣርቶ ዕርዳታው መሰጠት ጀምሯል። በዚህም መሠረት መቶ ዘጠና ሦስት አትሌቶች ተለይተው ድጋፉ እንደደረሳቸው ታውቋል። ዕርዳታው የሚሰጣቸው አትሌቶች ከሃምሳ ስምንት የዓለም አትሌቲክስ አባል አገራት ፌዴሬሽኖች የተለዩ ሲሆን እያንዳንዳቸው በመጀመሪያው ዙር ድጋፍ ሦስት ሺህ ዶላር እንደሚደርሳቸው ተጠቆሟል። የድጋፍ ጥያቄውን ለማቅረብ የተሰጠው ቀነ ገደብ ባለፈው የፈረንጆች ግንቦት ሰላሳ ቀን የተጠናቀቀ ሲሆን ሁለት መቶ ስልሳ አንድ አትሌቶች የድጋፍ ጥያቄውን አቅርበው ጉዳዩን የሚመረምረው የባለሙያዎች ቡድን በተቀመጠው መስፈርት መሠረት አጣርቶ መቶ ዘጠና ሦስት አትሌቶች ድጋፉን እንዲያገኙ ውሳኔ አሳልፏል። የባለሙያዎቹ ቡድን ድጋፉን ለመስጠት በዋናነት ከተመለከታቸው መስፈርቶች መካከል አንድ ድጋፍ የሚሻ አትሌት በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አገሩን ለመወከል የተመረጠ መሆን እንዳለበት፣ ለገጠመው የገንዘብ ችግር አሳማኝ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣ ካለፈው የውድድር ዓመት አኳያ የሚያገኘው ገቢ በእጅጉ የቀነሰና ከአበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ክስ ያልቀረበበት መሆን እንደሚገባው ጠቁመዋል። በተጨማሪም በየትኛውም የውድድር\nአይነት በዓለም አትሌቲክስ\nየደረጃ ሰንጠረዥ ከአንድ\nእስከ ስድስት ባለው\nውስጥ ስማቸው የሰፈረ\nአትሌቶች፣ በ2019 በየትኛውም\nየወርቅ ደረጃ ባለው\nየጎዳና ላይ ውድድር\nእስከ ስድስት ባለው\nደረጃ ያጠናቀቁ እንዲሁም\nበ2019 የዳይመንድ\nሊግ ውድድሮች እስከ\nስልሳ ሺህ ዶላር\nድረስ ሽልማት ያገኙ\nአትሌቶች የድጋፍ ጥያቄያቸው\nተቀባይነት እንደሌለው ታውቋል።\nድጋፉን የሚያገኙ አትሌቶች\nወይም አገራት ስም ያልተጠቀሰ ሲሆን ጥያቄያቸው ተመርምሮ ድጋፍ የሚደረግላቸው አትሌቶች በዚህ ሳምንት መጨረሻ ገንዘቡ እንደሚደርሳቸው ተጠቁሟል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት እንዲሁም የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ሊቀመንበር ሴባስቲያን ኮ ይህን ድጋፍ ለአትሌቶች ለመስጠት እንደታሰበ በሰጡት መግለጫ ወቅት እንዳስቀመጡት፣ የገንዘብ ድጋፉ ባለፉት ጥቂት ወራት ከውድድር በመራቃቸው ምንም አይነት ገቢ አጥተው የገንዘብ ቀውስ ውስጥ ለገቡ አትሌቶች ይውላል። እ.ኤ.አ በ1986 በሞናኮው ልዑል አልበርት ሁለተኛ አማካኝነት በአትሌቲክስ ስፖርት ለሚገጥሙ ችግሮች የበጎ አድራጎት ሥራዎችን ለማከናወን የተቋቋመው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ካለው በጀት ላይ ቀንሶ አትሌቶች በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለገጠማቸው ችግር ድጋፍ እንዲውል ማድረጉ ይታወቃል። ድጋፉን ለመስጠት ከተቋቋመው ኮሚቴ መካከል የቀድሞው የኦሊምፒክ የ1500 ሜትር አሸናፊው ሞሮኳዊ አትሌት ሂቻም ኤልግሩዥ፣ የምርኩዝ ዝላይ የዓለም ቻምፒዮኗ ካተሪና ስቲፋኒዲ (የዓለም አትሌቲክስ ኮሚሽንን ወክላ)፣ የዓለም አትሌቲክስ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሱኒል ሳብሃርዋልና ኤቢይ ሆፍማንና ሌሎችም ተካተዋል። ‹‹ሂቻም ኤልግሩዥ ይህን የድጋፍ ሃሳብ በማቅረቡና ልዑል አልበርት ይህን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ላበረከተው ጠንካራ ድጋፍ ላመሰግናቸው እወዳለሁ›› በማለት ሃሳባቸውን ያሰፈሩት ሴባስቲያን ኮ፣ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከዓለም አትሌቶች ጋር በተለያየ መንገድ የቅርብ ግንኙነት እንዳላቸው በመጠቆም ዓለም አቀፍ ውድድሮች በመሰረዛቸው በርካታ አትሌቶች የገቢ ምንጫቸው እንደ ደረቀና የገንዘብ ችግር እንደገጠማቸው አብራርተዋል። በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የዓለም አትሌቲክስ ውድድሮች በእጅጉ መጎዳታቸውን ያስታወሱት ኮ፣ አትሌቶች ገቢያቸው ከውድድር የሚያገኙት ሽልማት እንደመሆኑ በዓመቱ መጨረሻ የተወሰኑ ውድድሮችን በማካሄድ ስፖርቱንና አትሌቶቹን እንዳይዳከሙ የማድረግ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። አትሌቶችን ለመደገፍ አሁን ከተያዘው በጀት ባሻገር የስፖርት ቤተሰቡ በሚያደርገው ድጋፍ ተጨማሪ የረድኤት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ጠቁመዋል። ልዑል አልበርት ሁለተኛ\nበበኩላቸው ፋውንዴሽኑን ከመሠረቱ\nከሰላሳ አምስት ዓመታት\nበላይ እንደሆነ በማስታወስ\nየፋውንዴሽኑ አላማ አትሌቲክስን\nማበረታታትና ብሔራዊ አትሌቲክስ\nፌዴሬሽኖች እንዲሁም አትሌቶች\nበችግር ጊዜ የገንዘብ\nዋስትና እንዲኖራቸው ማድረግ\nመሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም\nመሠረት ፋውንዴሽኑ ባለፉት\nዓመታት ሰላሳ ሚሊየን\nዶላር ለተመሳሳይ አላማ\nእንዳዋለና አሁንም አትሌቶች\nበሚቸገሩበት በዚህ ወቅት\nሊደርስላቸው በመቻሉ የተሰማቸውን\nደስታ ገልፀዋል። ይህ\nድጋፍ አትሌቶች ኦሊምፒክን\nጨምሮ ለዓለም አቀፍ\nውድድሮች የሚያደርጉትን ዝግጅት\nእንዳያቋርጡና በገጠማቸው ችግር\nውጥረት ውስጥ እንዳይገቡ\nሊረዳቸው እንደሚችልም አክለዋል። የቀድሞው የ1500 ሜትር የዓለም ክብረወሰን ባለቤትና የድጋፉ ሃሳብ አመንጪ አትሌት ኤልግሩዤ በበኩሉ፣ የኮሮና ቫይረስ በሁሉም ዓለም ሕዝብ ላይ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ እንዳሳደረ በማስታወስ ሁሉም የዓለም ሕዝብ ይህን ችግር ለመጋፈጥ በጋራ የሚቆምበት ወቅት አሁን መሆኑን አብራርቷል። የዓለም አትሌቲክና ፕሬዚዳንቱ የድጋፍ ሃሳቡን በቅንነት ስለተቀበሉትም ምስጋናውን አቅርቧል። ዓለም አቀፍ ውድድሮች በመታገዳቸውም በርካታ አትሌቶች ሊደርስባቸው የሚችለውን የኢኮኖሚ ጫና በማሰብ ይህን በጎ ተግባር መፈፀም እንደሚያኮራም ተናግሯል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 18/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "75d675f81bcb7e190c21aebd0b8a2bb8" }, { "passage": "በአትሌቲክስ ስፖርት ትልቁ ውድድር ዓለም ሻምፒዮና፤ የኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ አትሌቶች በሚያስመዘግቡት ውጤት በደረጃ ሰንጠረዡ አናት ከሚቀመጡት አሥር ሀገራት መካከል ይገኛሉ። ይህም አህጉሪቷ በአትሌቲክስ ስፖርት የተሻለ እንቅስቃሴ አላት ለማለት ያስችላል። የኢትዮጵያ እና ኬንያ ደረጃ ደግሞ በተለይ በምስራቅ አፍሪካ ስላለው የስፖርቱ ሁኔታ በግልጽ የሚያሳይ ነው። በቀጠናው ስፖርቱን የሚመራው አካልም የተሻለ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ካሉት ማህበራት ይመደባል።የማህበሩ አባላት ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ በአዲስ አበባ መገናኘታቸው ይታወሳል። በስብሰባው ላይም የኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን ርስቱ ይርዳው፣ የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሃማድ ካልካባ ማልቡም፣ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር /አይደብልኤፍ/ ተወካይ ጂ ኢስራም፣ የማህበሩ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ጃክሰን ቱዋይ እንዲሁም የማህበሩ አባል ሃገራት ተወካዮች ተገኝተዋል።\nበዕለቱ ከተያዙት አጀንዳዎች መካከል አንዱ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላትን መምረጥ ነበር። በምርጫውም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮሎኔል አትሌት ደራርቱ ቱሉ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆና በሙሉ ድምፅ ተመርጣለች። አትሌት ደራርቱ ከዚህ ባሻገርም በአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ውስጥ ማህበሩን በመወከል የቦርድ አባል ሆና ተመርጣለች።ማህበሩ ከሁለት ዓመታት በፊት በቀድሞው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ አለባቸው ንጉሴ ይመራ ነበር። እሳቸው ከፌዴሬሽኑ ሥራ አስፈጻሚነት መነሳታቸውን ተከትሎም ማህበሩ፤ ጃክሰን ቱዋይ በተባሉት ኬንያዊ በጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ሲመራ ቆይቷል።\nበቅርቡም በኤርትራዋ አስመራ በተደረገው ጉባኤ ምርጫውን በኢትዮጵያ ለማድረግ በተያዘው ቀጠሮ መሰረት ባሳለፍነው ቅዳሜ ተካሂዷል። በዚህም ጃክሰን ቱዋይ በፕሬዚዳንትነታቸው እንዲቀጥሉ እና ምክትላቸውም ሻለቃ አትሌት ደራርቱ እንድትሆን ተወስኗል።\nበምርጫው የኢትዮጵያ ሥራ አስፈጻሚ ውስጥ መግባት ሃገሪቷ በዘርፉ ያላትን ተሰሚነት እንደሚጨምር ይጠበቃል። ሃገሪቷ በአህጉር እና በዓለም አቀፎቹ ማህበራት በአመራርነት ለሚኖራት ሚናም የተሻለ መንገድ ይከፍትላታል። ሌላው በአመራርነት የመገኘት ጥቅሙ ተናግሮ የማሳመን እድልን የሚያስገኝም ይሆናል።ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር 215 አባል ሀገራት ያሉት ሲሆን፤ በአወቃቀሩ መሰረት አባል ሀገራቱ በስሩ ባሉት ስድስት ማህበራት ይመራሉ። ከማህበራቱ መካከል አንዱ የሆነው ደግሞ የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ነው። መቀመጫውን በሴኔጋሏ ዳካር ያደረገውና በካሜሩናዊው ፕሬዚዳንት ሃማድ ካልካባ ማልቡም በሚመራው ኮንፌዴሬሽን ሥርም፤ በቀጠና የተከፋፈሉ አምስት ማህበራት ይገኛሉ።የመጀመሪያው የሰሜን (ሳህራ) ቀጠና ሲሆን፤ አራት ሀገራትን በአባልነት ይይዛል። በኒጀር ወይም በምዕራቡ ቀጠና ደግሞ 16 ሀገራት ይገኛሉ። የምስራቅ (ናይል) ቀጠና 10 ፣ በመካከለኛው አፍሪካ ቀጠና 10 እንዲሁም በደቡብ (ካልሃሪ) ቀጠና 14 ሀገራት በአባልነት ታቅፈው ይገኛሉ። ማህበራቱ በቦርድ የሚመሩ ሲሆን፤ የራሳቸው ኮሚቴ፣ ዓመታዊ ስብሰባ እንዲሁም የሚመሩበት መርሃ ግብርም አላቸው። ከዓለም አቀፉ ማህበር በሚመደብላቸው በጀትም ስልጠናዎችን እና ውድድሮችንም ያዘጋጃሉ። የምስራቅ አፍሪካው ማህበርም እነዚህን በመተግበር ከሌሎች የስፖርት ተቋማት አንጻር የተሻለ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ የሚገኝ ነው። ኢትዮጵያም ማህበሩን በመምራት ረገድ የተሻለ ተሞክሮ ያላት ሲሆን፤ ወይዘሮ ብስራት ጠናጋሻው እና አቶ አለባቸው ንጉሴ ከዚህ ቀደም በፕሬዚዳንትነት ማህበሩን የመሩ ኢትዮጵያዊት ናቸው።አዲስ ዘመን ጥር 7/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "21f04f9cfa3b54b5b75fbed19520a7cd" }, { "passage": "የዓለም ታላላቅ ስፖርት መድረኮች በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ምክንያት ለበርካታ ወራት ከቆሙበት ለመቀጠል ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ለመመልከት ተችሏል። የእግር ኳሱ ዓለም ታላላቅ ሊጎች በዝግ ስቴድየምም ቢሆን ጨዋታዎችን እያስቀጠሉ ካንቀላፉበት እየነቁ ይገኛሉ። በዚሁ ወረርሽኝ ሳቢያ ክፉኛ የተጎዳው የዓለም አትሌቲክስ እንቅስቃሴም ከጥቂት ወራት በኋላ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለመመለስ ከወዲሁ እንቅስቃሴ መጀመሩ ለዓለማችን አትሌቶች መልካም ዜና ሆኗል። በተለይም የዓለማችን ኮከብ አትሌቶች በጉጉት የሚጠብቁት ዓመታዊው የዳይመንድ ሊግ ውድድር እንደሚመለስ መገለፁን ተከትሎ ለወራት ከውድድር ርቀው ለተቀመጡት አትሌቶች የምሥራች መሆኑ አይቀርም። በኮሮና ቫይረስ\nወረርሽኝ\nየተነሳ\nየዓለም\nአትሌቲክስ\nዓመታዊ\nመርሃግብሮች\nበተያዘላቸው\nጊዜ\nሳይካሄዱ\nበመቅረታቸው\nተዘበራርቀዋል።\nየዓለም\nአትሌቲክስ\nይህንን\nለመካስም\nበጊዜያዊነትም\nቢሆን\nእንደ\nዳይመንድ\nሊግ\nያሉ\nውድድሮች\nመርሃግብርን\nለመከለስ\nተገዷል።\nበብራሰልስ\nየሚካሄደውም\nውድድር\nከተከለሱት\nመርሃግብሮች\nመካከል\nየሚጠቀስ\nነው።\nዳይመንድ\nሊጉ\nወደ\nውድድር\nሲመለስ በመጪው የፈረንጆች መስከረም ወር መጀመሪያ እንደሚካሄድ የሚጠበቀው የብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ከወዲሁ ትኩረት አግኝቷል። እንግሊዛዊው የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮናዎች ጥምር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ አትሌት ሞሐመድ ፋራህ ከ2017 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ መም ውድድሮች ተመልሶ በብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ተፎካካሪ እንደሚሆን መናገሩን ተከትሎ ውድድሩ ትኩረት ማግኘት ችሏል። የሰላሳ ሰባት ዓመቱ ፋራህ ወደ ውድድር ከመመለሱ በተጨማሪ በ21 ነጥብ 285 ኪሎ ሜትር ፉክክሩን ከአንድ ሰዓት በታች ለማጠናቀቅና አዲስ የዓለም ክብረወሰን ለማሻሻል መዘጋጀቱን ተከትሎ የብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ከወዲሁ በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጓል። የርቀቱ ክብረወሰን በጀግናው አትሌት ሃይሌ ገብረሥላሴ የተያዘ ሲሆን ከአስራ ሦስት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ 2007 ኦስትራቫ ላይ ማስመዝገቡ ይታወሳል። በብራሰልሱ ውድድር የአውሮፓ የአስር ሺህ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊው አትሌት በሽር አብዲ ከፋራህ ጋር እንደሚፎካከር የተገለፀ ሲሆን ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን የርቀቱ ፈርጦችም በቅርቡ ውድድሩን እንደሚቀላቀሉ ይጠበቃል። ‹‹ከልምምድ አጋሬ\nበሽር አብዲ ጋር\nውድድሩን ከአንድ ሰዓት\nበታች በማጠናቀቅ የዓለም\nክብረወሰን ለማስመዝገብ እየተዘጋጀን\nነው፣ ይህ ለእኔ\nትልቅ አጋጣሚ ነው፣\nበብራሰልስ ከዚህ ቀደም\nባደረኳቸው ውድድሮች ጥሩ\nትዝታዎች አሉኝ፣ ብራሰልስ ላይ ፈታኝ ሰዓት መሮጥ ይቻላል፣ ሁሉም ነገር ቀላል ነው›› በማለት ፋራህ ለመገናኛ ብዙሃን አስተያየቱን ሰጥቷል። በተመሳሳይ በሴቶች መካከል\nበሚካሄደው ውድድር ግን\nኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተፎካካሪ\nከመሆን ባለፈ አዲስ\nየዓለም ክብረወሰን ለማስመዝገብ\nመዘጋጀታቸውን የውድድሩ አዘጋጆች\nገልፀዋል። በዚህም አትሌት\nአባብል የሻነህ እና\nብርሃኔ ዲባባ ተጠባቂ\nሆነዋል። 18 ነጥብ\n517 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው\nውድድር የዓለም ክብረወሰን\nየተመዘገበበት ጊዜ ከአስራ ሁለት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ 2008 ላይ ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድሬ ቱኔ የክብረወሰኑ ባለቤት መሆኗ አይዘነጋም። በዚህ የውድድር ዓመት የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰንን በ1፡04፡31 ሰዓት መስበር የቻለችው አባብል የሻነህ ለአስራ ሁለት ዓመታት ያልተደፈረውን የድሬ ቱኔን ክብረወሰን እንደምታሻሽል ግምት የተሰጣት ሲሆን በማራቶን 2፡18፡35 የሆነ የራሷ ምርጥ ሰዓት ያላት ብርሃኔ ዲባባም ብራሰልስ ላይ ለክብረወሰን ተጠባቂ ሆናለች።አዲስ ዘመን ሰኔ 20/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "a9d8021a3c08aa13dd1f9158c959625e" } ]
6962d4ef1030ae85a4ba4af08a35f54c
c7359f79daf14553b513a2b8d155ceab
ኮቪድን ለመከላከል የስፖርት ቤተሰቡ ርብርብ ቀጥሏል
በመላው ዓለም የኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ-19) ለመዋጋት የሚደረገው ርብርብ እንደቀጠለ ነው። በኢትዮጵያም የስፖርት ቤተሰቡ ተሳትፎ ገና ከጅምሩ አበረታች የሆነ መንገድ ያሳየ ሲሆን፤ እውቅ ስፖርተኞችና የስፖርት ማህበራት ድጋፋቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል። የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ክለቦችና ተጫዋቾች በገንዘብና በዓይነት ድጋፋቸውን በመስጠት ላይ ካሉት መካከል በግምባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ። የሃዲያ ሆሳዕና እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞችና የጽህፈት ቤት ሰራተኞች የደመወዛቸውን 50 በመቶ መስጠታቸውን ሶከር ኢትዮጵያ አስነብቧል። በዚህም 443 ሺ 366 ብር ስርጭቱን ለመቆጣጠር ለሚቋቋመው ግብረ ኃይል አበርክቷል። የጅማ አባጅፋር እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች እና አጠቃላይ የክለቡ ሠራተኞች 130 ሺ ብር ድጋፍን አድርገዋል። የድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾችና አባላት በበኩላቸው ሙሉ ደመወዛቸውን ለዚሁ ዓላማ እንዲውል ውሳኔ ላይ መድረሳቸው ታውቋል። የሲዳማ ቡናው አጥቂ አዲስ ግደይ፣ የመከላከያው አጥቂ ሀብታሙ ወልዴ፣ የጅማ አባጅፋሩ አማካይ ንጋቱ ገብረስላሴ፣ የሃላባ ከተማው ልመንህ ታደሰ እና የጅማ አባጅፋር ተከላካይ መላኩ ወልዴ በጋራ ለትውልድ ከተማቸው አጋሮ በጥሬ ዕቃ ድጋፋቸውን አድርገዋል። በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች 80 ሺ ብር የሚገመት የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ማስረከባቸውን ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ በተጨማሪም ቆሼ ተብሎ ወደ ሚጠራው ስፍራ በመጓዝ ለ541 አቅመ ደካሞች ርዳታ ሰጥተዋል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ኮሚሽኑን ጨምሮ በስሩ የሚገኙ የስፖርት ማህበራት ድጋፋቸውን አጠናክረው ከቀጠሉት መካከል ይገኛሉ። በከተማው የውሹ ፌዴሬሽን 45 ሺ 800 ብር በከተማ ደረጃ ለተቋቋመው ኮሚቴ የሚውል ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ስፖርት ኮሚሽነር አበርክቷል። ከዚህም ውስጥ በስራ አስፈፃሚው ውሳኔ ፌዴሬሽኑ 20 ሺ ብር፣ 15 ሺ 800 ብር እና የምግብ ግብዓቶች ከክለብ አሰልጣኞች እንዲሁም የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ማስተር ፍሬህይወት ሽታዬ በግላቸው 10 ሺ ብር አበርክተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽንም በስሩ ያሉ ማዕከላትን እስከ ታችኛው የወረዳ መዋቅር ድረስ ለቅድመ መከላከልና መቆጣጠር ለሚያስፈልጉ ተግባራት ሁሉ እንዲውሉ መወሰኑ ይታወቃል። ከዚህ መካከል አንዱ የሆነው የጃን ሜዳ ስፖርት ማዕከል በጊዜያዊነት ወደ አትክልት ተራነት ተዘዋውሮ ከዛሬ ጀምሮ አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል።አዲስ ዘመን መጋቢት 27/2012ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29814
[ { "passage": "የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ለመዋጋት የስፖርት ቤተሰቡንና ባለድርሻ አካላት በማሳተፍና በማስተባበር ጠንካራ ሥራዎችን መስራቱን አስታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከትናንነት በስቲያ የአዲስ አበባ ከተማ ስፖርት ኮሚሽን የ2012ዓ.ም በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻፀምን ሲገመግም ፤የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳዊት ትርፉ፤ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ለመዋጋት የስፖርት ቤተሰቡንና ባለድርሻ አካላት በማሳተፍና በማስተባበር ጠንካራ ሥራዎችን መስራቱን አስታውቀዋል። «ዓለም አቀፍ ስጋት የሆነው ኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ከመደበኛ ሥራው ትይዩ ቫይረሱ ከተከሰተ ጀምሮ በከተማ አቀፍ ደረጃ ወረርሽኙን ለመዋጋት እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል። የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ለመዋጋት የስፖርት ቤተሰቡንና ባለድርሻ አካላት በማሳተፍና በማስተባበር ጠንካራ ሥራዎቹን አከናውኗል»ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩን ጥሪን መሰረት በማድረግ የኮቪድ -19 ወረርሽኝ በህብረተሰባችን ላይ የሚደርሰውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለማቃለል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለወገኖች የገንዘብ ፣ ለምግብነት የሚውሉ ቁሳቁሶች ፣ ንፅህና መጠበቂያ ዕቃዎች ፣የደም ልገሳና የበጎ ፈቃደኛ አገልግሎቶች በመሥጠት ትልቅ ስራ መሰራቱን ገልፀዋል ።ከዚህ ባሻገር ራሳቸውን ከኮረና ቫይረስ ለመጠበቅ በቤታቸው ለሚገኙ የጋራ መኖሪያ ( ኮንዶሚኒየም) ነዋሪዎች በቤታቸው ሆነው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተደራሽ በማድረግ ኮሚሽኑ ወረርሽኙን ለመዋጋት እየተደረገ ባለው ርብርብ ላይ የጎላ ተሳትፎ ማድረጉን ተናግረዋል። ስፖርት ኮሚሽኑ በ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ቁልፍና አበይት ዕቅዶችን ያወጣ እንደመሆኑ ወረርሽኙ ወደ በሀገራችን ከመከሰቱ ቀደም ብሎና በተከሰተበት ወቅት የተለያዩ ተግባራትን ማከናወኑን የገለጹት አቶ ዳዊት፤በዋናነት በታዳጊ ወጣቶች ስልጠና መርሀ ግብር፣ በማስ ስፖርት (በማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ)፣በውድድርና ተሳትፎ፣ በተቋማዊ ለውጥ ሥራ፤ የስፖርት የልማት ስራዎችና ግንባታ ክትትል ላይ ትኩረት መሰጠቱን አብራርተዋል። የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ለቋሚ ኮሚቴው የዘጠኝ ወራቱን እቅድ አፈጻፀምን ለቋሚ ኮሚቴው ከማቅረቡ በፊት በከተማ እየተገነቡ ከሚገኙ የስፖርት ማዘውተሪያዎች መካከል በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኙትን ሶስት ማዘወተሪያ ስፍራዎች ላይ የመስክ ምልከታ አካሂዷል። ቋሚ ኮሚቴው የስፖርት ኮሚሽኑን የዘጠኝ ወራት ተግባርን በጽሁፍና በመስክ ምልከታው ያደረገውን ግምገማ መሰረት በማድረግ አስተያየት የሰጠ ሲሆን፤ ኮሚሽኑ በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸው ተግባራት እጅግ የሚያስደስቱና የሚበረታቱ መሆኑን አመልክቷል። ኮሚሽኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል ሲያደርግ የነበረው እንቅስቃሴ፣በመዲናዋ ያለውን የስፖርት ማዘውተሪያ እጥረት ለመቅረፍ ትኩረት በማድረግ የተሰሩ ስራዎችን አድንቋል።በዘጠኝ ወራት የታዩትን ጠንካራ ተግባራትን አስቀጥሎ የነበሩትን ጉድለቶችን አስወግዶ በቀጣይ ጊዜያት የተሻለና አመርቂ ሥራ መስራት ይገባል ሲል ቀጣይ የስራ አቅጣጫን አስቀምጧል።አዲስ ዘመን ግንቦት 21/2012 ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "ea70503fddd130e3fcd56d114ad71d08" }, { "passage": "ስፖርት የሰላም፣ ፍቅር፣ የአብ ሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየት ኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲ ካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብዓዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን የአለም ህዝብ እየፈተነ ባለው የኮሮና ወረርሽኝን ለመዋጋት ሲደረግና እየተደረገ ባለው ርብርብ ላይ በስፖርት ቤተሰቡ በኩል የታየው ተሳትፎ ትልቅ ማሳያ ይሆናል።የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የአለም ህዝብን እንደ ቅጠል ከማርገፍ በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ላይ ይህ ቀረሽ የማይባል መቃወስን አስከትሏል።የስፖርት ኢንደስትሪው ደግሞ\nዋነኛ ሠለባ ከሆኑ\nመስኮች በግንባር ቀደምነት\nይጠቀሳል። የቫይረሱ ስጋትነት\nበዓለም አቀፉ የጤና\nተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ\nጀምሮ፤ ውድድሮች ተቋርጠዋል፤\nተሰርዘዋል። ይህን ተከትሎ\nየአለምን ኢኮኖሚ በማንቀሳቀስ\nረገድ ግንባር ቀደም\nተጠቃሽ የሆነው የስፖርት\nኢንደስትሪውን በአጭር ጊዜ\nለከፍተኛ የፋይናነስ ቀውስ\nዳርጎታል።በአለም ስፖርት ላይ\nየተፈጠረው ከፍተኛ መቃወስ\nግን የስፖርቱን ማኅበረሰብ\nየሰብዐዊነት ውሃ ልክ\nከመሆን አላደናቀፈውም ነበር።የስፖርት\nቤተሰብ በወረርሽኙ ጉዳት\nከመቆዘም ይልቅ ,፤\nየሰብዐዊነት ጋሻን በማንሳት\nአለምን ከጭንቅ ለማውጣት\nበሚደረገው ርብርብ ሰፊ\nተሳትፎ ሲያደርግ ነበር፤እያደረገም\nይገኛል። በስፖርቱ መስክ\nዓለም አቀፍ ዝናን\nካተረፉ ግለሰቦች እስከ\nዓለም አቀፍ ተቋማት\nድረስ ወረርሽኙን ለመመከት\nእየተደረገ ባለው ርብርብ\nሲያደርጉ የነበረው ተሳትፎ\nትልቅ ቦታ አጊንቷል።የስፖርቱ\nዘርፍ ባለድርሻ የሚባሉት\nአካላት በተናጠልና ተቋማዊ\nበሆነ መልኩ ድጋፍ\nለሚሹ ድጋፍ በማድረግ\nእንዲሁም ገንዘብ በማሰባሰብ\nወረርሽኙን የመዋጋት ሂደቱን\nበፊት አውራሪነት ሲመሩ\nታዝበናል።በተለያዩ ሀገራት ዓለም\nአቀፉን ወረርሽኝ ለመዋጋት\nበስፖርቱ ማኅበረሰብ ዘንድ\nየታየው ተሳትፎ በሀገራችንም\nተመሳሳይ ሲሆን ታዝበናል። በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ይፋ ከተደረገበት ከወርሃ መጋቢት መጀመሪያ አንስቶ የስፖርቱ ማህበረሰብ ድርሻ ግዙፍ ነው። በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የስፖርት ማህበራት፣ ተጫዋቾች፣ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በዘመነ ኮሮና የስፖርቱ ማኅበረሰብ ሰብዐዊነትን መሰረት ያደረገው እንቅስቃሴ እንደቀጠለ ይገኛል። በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረውን «ማዕድ ማጋራት» መርሃ ግብር ሶስተኛው ዙር ከትናንት በስቲያ በአዲስ አበባ ትንሿ ስታዲየም ተጀምሯል።የስፖርቱ ማኅበረሰብ ህዝባዊነት\nየሚያረጋግጥ መሆኑ የተነገረለት\nሶስተኛው ዙር ማዕድ\nየማጋራት መርሃ ግብር\nሲጀመር ፤ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ\nስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር\nአቶ ኤሊያስ ሽኩር\nእንደተናገሩት፤ የኮሮና ቫይረስ\nወረርሽኝ መከሰት የመደጋገፍ\nእና የመረዳዳት የቀደመ\nባህላችንን የበለጠ እንዲጎለብት\nአድርጓል።የኮሮና ቫይረስ ወደ\nሀገራችን ከገባ ጀምሮ\nወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር\nየስፖርቱ መንግስታዊ እና\nህዝባዊ አደረጃጀቶች፣ ታዋቂ\nአትሌቶች፣ የደጋፊ ማህበራት፣\nበአጠቃላይ የስፖርት ቤተሰቡ\nህብረተሰቡን በማንቃት እና\nኢኮኖሚያዊ ጫናውን ለመቋቋም\nየሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ\nበማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን\nበመጣት ላይ ያደረጉትን\nተሳትፎ ጠቅሰዋል። የስፖርቱ\nማኅበረሰብ ድጋፍ ተጠናክሮ\nየሚቀጥልና የምገባ መርሃ\nግብሩ መጀመር ለዚሁ\nማሳያ ይሆናል ብለዋል።\nየጎዳና ላይ የሚገኙ\nወገኖቻችንን በተወሰነ መልኩ\nለማገዝ አንድ ወር\nየሚቆይ የምገባ መርሃ\nግብሩ ይሄንኑ ሚና\nመሰረት ባደረገ መልኩ\nመጀመሩን የተናገሩት አቶ\nኤልያስ፤ በስታዲየም ዙሪያ\nመርሃ ግብሩ እንዲደረግ\nየተመረጠበትን ምክንያት መኖሩን\nአመልክተዋል። «በወቅታዊ የኮሮና\nወረርሽኝ ምክንያት ስርጭቱን\nለመቆጣጠር ሲባል በተለይ\nስታዲየም ዙሪያ የሚገኙ\nባር እና ሬስቶራንቶች\nመዘጋታቸው እና በአካባቢው\nያለው እንቅስቃሴ መቆሙ\nይታወቃል። ሬስቶራንቶች መዘጋታቸውን ተከትሎ\nከሬስቶራንቶች ተመላሽ የሚሆኑ\nምግቦችን ይጠቀሙ የነበሩ\nየጎዳና ተዳዳሪዎችም ሆነ\nበስታዲየም አካባቢ የተለያዩ\nነገሮችን በመሸጥ ይተዳደሩ\nየነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች\nለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።\nበመሆኑም ጊዜው የከፋ\nችግር ላጋጠማቸው የህብረተሰብ\nክፍሎች እጃችን የምንዘረጋበት፤\nየጋራ መከራችንን በመተጋገዝ የምናልፍበት መሆኑን በማመን እና ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ነው »ሲሉ አብራርተዋል። አቶ ኤልያስ በመጨረሻ የተጀመረው ተግባር የሚቋረጡ ሳይሆን በቀጣይም እነዚህ ወገኖቻችን በዘላቂነት ህይወታቸውን ሊመሩበት በሚችሉ ጉዳዮች ላይ የስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ አቅሙ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የቢጂ አይ ኢትዮጵያ አመራሮች በጋራ በመሆን ባስተላለፉት መልዕክት ደግሞ፤ የምገባ መርሃ ግብሩ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።በስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት የተጀመረው ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብሩ 3ኛ መጀመሩን በዘመነ ኮሮና የስፖርቱ ማኅበረሰብ ሰብዐዊ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ያመላክታል ተብሏል።ሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረው ሶስተኛው ዙር «ማዕድ ማጋራት» መርሃ ግብሩ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል እንደሚመገቡ ታውቋል።በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ከቢ. ጂ አይ ኢትዮጵያ በጋራ በመሆን የመጀመሪያው ዙር ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወራት የዘለቀ ነበር።የስፖርት ተቋማቱ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ ማጋራት ብሄራዊ ጥሪን»ተከትሎ መርሃ ግብሩን የጀመሩት ሲሆን፤ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል በመመገብ ሀሳቡን ተግብረውታል።ሁለተኛ ዙር ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወር ያህል ተግባራዊ ተደርጎ በመጠናቀቁ ፤ሶስተኛው ዙር መርሃ ግብር ከሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 16 ቀን 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን በምገባ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ እንደሚደረጉ ታወቋል።በ3ኛው ዙር የምገባ ፕሮግራም የኢትዮጵያ መድን ድርጅት 600 ሺ ብር ድጋፍ በማድረግ የወገን አጋርነቱን ማሳየቱ ተነግሯል። የምገባ መርሃ ግብሩን\nለሶስተኛው ዙር ማስቀጠል\nመቻሉ የስፖርቱ ማህበረሰብ\nበዘመነ ኮሮና ማህበራዊ\nኃላፊነትን በመወጣት እንደ\nከዚህ ቀደሙ ሁሉ\nየተጠናከረ ተሳትፎ እያደረገ\nመሆኑን አመላካች ሆኗል።\nየመርሃ ግብሩ ተግባራዊነት\nጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ\nአህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ\nማጋራት ብሄራዊ ጥሪን»\nወደ መሬት ከማውረድ\nበተጨማሪ፤ ስፖርት -ሰብዐዊነትን\nጋሻ ያደረገ ማኅበራዊ\nክዋኔ መሆኑን በተግባር\nእንዲረጋገጥ ያረጋገጠ መሆኑን\nብዙዎች መስክረውለታል።አዲስ\nዘመን ሰኔ 19/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "a05aeb114450545a22415d9f42e50c22" }, { "passage": "በዓለማችን ብሎም በሀገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ለሚደረገው ርብርብ የመከላከያ እግርኳስ ክለብ የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።የአዋቂ የወንዶች፣ ሴቶች ቡድን እና የአሰልጣኝ አባላት በጋራ በመሆን 210 ሺህ ብር ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት ያስረከቡት። ይህ ድጋፍ በሲቪል እግርኳስ ቡድኑ ይደረግ እንጂ በቀጣይ ቀናት የወታደር እግርኳስ ቡድን መሰል የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚችል ሰምተናል።ወረርሽኙን ተከትሎ የሚመጡ ማኀበራዊ ችግሮችን አስቀድሞ መከላከል ይቻል ዘንድ በስፖርቱ ዘርፍ በሁሉም አቅጣጫ የሚደረገው እርብርብ በቀጠለበት በአሁኑ ሰዓት በቀጣይም መሰል ትብብሮች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚችሉ መረጃዎች እየጠቆሙ ይገኛል።", "passage_id": "8aa332c68d3cdc7e405c03e313326c0e" }, { "passage": " የቅዱስ ጊዮርጊስና የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ስታድየም አካባቢ ለሚገኙ የጎዳና ተዳዳሪዎች ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ድጋፍ አደረጉ። የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ኮሮና ቫይረስን በጋራ ለመከላከል ይቻል ዘንድ ለበርካታ የጎዳና ተዳዳሪዎች ቫይረሱን ሊከላከሉ የሚችሉበትን የማክስ እና የሳሙና ድጋፍ አድርገዋል። የሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች ከትናንት በስቲያ በአዲስ አበባ ስታድየም በነበረው ልዩ ፕሮግራም ላይ እስከ 350 ለሚደርሱ የጎዳና ተዳዳሪዎች ምሳ አብልተዋል። በምሳ ማብላት መርሃ ግብሩ ላይም ኮሮና ቫይረስን እንዴት መከላከል እንደሚቻል የግንዛቤ ማስበጫ ትምህርት ተሰጥቷል። «መርሃ ግብሩ የተዘጋጀበት ዋና ዓላማም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለጎዳና ተዳዳሪዎች እንደሌላው ማህበረሰብ ‹በአሁን ወቅት ማን አለላቸው› በሚል ከእነሱ ጎን ለመቆም ነው » ሲሉ የክለቦቹ ደጋፊ ተወካዮች ገልጸዋል። በተጨማሪም ከሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች የተሰባሰበው የገንዘብ እርዳታም ገቢው ለእነዚህ የጎዳና ተዳዳሪዎች ሆኖ የመጪውን የፋሲካ በዓል በሌላ ልዩ ፕሮግራም እንዲያሳልፉበት እንደሚደረግ ተገልጿል። የስፖርት ማህበረሰቡ ወገናዊነት በቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች እንደተፈጸመው ሁሉ፤ በሌሎች ማህበራትም በኩል ተግባሩ ተጠናክሮ መቀጠሉን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ አሰልጣኞች ይፋዊ ፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በእግር ኳስ ስፖርት የሚገኙ አሰልጣኞች የኮሮና ቫይረስን ለመቆጣጠርና ለማጥፋት እየተደረገ ባለው ርብርብ በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን ጽፏል። በመሆኑም በእግር ኳስ ሙያ ውስጥ የሚገኙ አሰልጣኞች ድጋፎቹን እስከ ሚያዚያ 06 ቀን 2012 ዓ.ም ረፋድ ድረስ ሲደረግ የነበረ ሲሆን ፤በዚህም 118 ሺ 500 ብር በመሰብሰብ ለሚመለከተው የመንግስት አካል ገቢ ሊደረግ መሆኑ መረጃው አመልክቷል። በዓለማችን የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከልና ለመግታት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተደረገ ላለው ርብርብ የስፖርት ማህበረሰቡ እያደረገ ያለውን አበርክቶ አጠናክሮ መቀጠሉን የሚያስረዳ ተግባር ሆኗል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 6/2012", "passage_id": "5ee50a82042d7ab643a57d751bba12ed" }, { "passage": "ቶክዮ የ2020 ኦሎምፒክ ውድድሮችን ለማከናወን ሁሉን አሰናድታ ዝግጅቷን ማልዳ ብትጨርስም፣ እንደ እንግዳ ደራሽ የሆነው ኮቪድ 19 ኮሮና ቫይረስ በመጨረሻው ሰዓት ድግሷን እንዳይሆን አድርጎታል። ይህም ብቻ አይደለም፣ ለውድድሩ ራሳቸውን በሚገባ እያዘጋጁ የነበሩ፣ ለድልም መንፈሳቸውን ያበረቱ አትሌቶችን ምኞትና ፍላጎት አደብዝዟል። ምንም እንኳ በ2021 ውድድሮች መካሄዳቸው አይቀርም ቢባልም፣ በአስጊነት ማማ ላይ የተቀመጠው ወረርሽኙ በቀጣይ ዓመትስ እንደማይኖር፣ እንደሚጠፋ ምን ዋስትና አለ እየተባለ ነው።ታድያ የወረርሽኙ ስጋት አስቀድሞ ባጠላባቸው አውሮፓ አገራት እግር ኳሱም ተመሳሳይ እጣ ነው የገጠመው። ሁሉም በሚባል ደረጃ ጨዋታዎች የተቋረጡ ሲሆን፣ እስከ ቅርብ ጊዜም ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝመው ነበር። ውድድሮቹ የሚቋረጡ ከሆነ የዓመቱ አሸናፊ ማን ይሆናል? ከታችኛው ከሚባለው ምድብ (ዲቪዚዮን) የሚገኙና ለማደግ ብዙ ወጪ አውጥተው ዓመቱን የተጫወቱ፣ በሊጉ ደግሞ ባላቸው ዝቅተኛ ነጥብ ወደ ታችኛው ምድብ የሚወርዱና መሰል ኹነቶች በቫይረሱ ምክንያት ተዛብተዋል።ታድያ ውድድሮች የሚሰረዙ ከሆነ ዓመቱ እንዳልነበረ ሙሉ ለሙሉ የማጥፋት ያህል የሚቆጠር ነው፣ ለእግር ኳስ ቤተሰብ። ይህ እንዳይሆንም ብዙ ሙግትና ክርክሮች የተካሄዱ ሲሆን፣ የአውሮፓ እግር ኳስ እንቅስቃሴ የጀመረ ይመስላል። የጀርመን ቡንደስ ሊጋም በዚህ ቀዳሚውን እርምጃ ወስዷል። ከኹለት ወር በኋላ በዘመነ ኮሮና የመጀመሪያውን የእግር ኳስ ጨዋታ በዝግ ስታድየም አካሂዷል። ቦርስያ ዶርትሙንድ እና ሻልካ ባደረጉት በዚህ ጨዋታም ዶርትሙንድ አራት ለባዶ አሸንፏል። ደስታው ግን እንደ ወትሮው አይደለም።ይህን በሚመለከት ከቀናት በፊት አልጀዚራ ባስነበበው ዘገባ፣ የጀርመኑ ሊግ ውድድር ይጀምር እንጂ የቀደመ መልኩ ጠፍቷል። ተጫዋቾች ለብቻቸው እንጂ አብረዋቸው ወደ ሜዳ የገቡ ሕጻናት ልጆች የሉም፣ መነካካት አይታሰብም፣ ከዳኞች ጋር መጨባበጥም እንደዛው፣ ጎል አግብቶ መተቃቀፍ ቀርቷል። ጨዋታው ሲደረግ ከክለቦቹ አስፈላጊ ሰዎች፣ እሳት አደጋ ሠራተኞችና ጥቂት ፖሊሶች፣ የስታድየም ጠባቂዎችና ጋዜጠኞች ብቻ ግን ይገኛሉ። በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ማተናገድ በለመደው በግዙፍ ስታድየም ውስጥ ሦስት መቶ ሰዎች ብቻ ተገኝተዋል።በሜዳው ጭንብል ከማድረግ ጀምሮ ተገቢው ጥንቃቄ ሁሉ እንዲደረግ ይጠበቃል። አሠልጣኞች ጮኸው መልእክት ማስተላለፍ ከፈለጉም 1.5 ሜትር ርቀት ላይ ሲሆኑ ብቻ አፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብላቸውን ማውለቅ ይችላሉ። ተቀያሪ ተጫዋቾች ደግሞ ተራርቀው ይቀመጣሉ። ከዛም በላይ አንድም ደጋፊ በስታድየሙ ውስጥ አይገኝም። በጥቅሉ እግር ኳስ ውበቱን በወረርሽኙ ተነጥቋል ማለት ይቻላል። ግን እንዳሉት ከሆነ ምንም ጨዋታ ካለማድረግ እንዲህ ባለ መልኩም ቢሆን መቀጠሉ ይሻላል። በዚህ የማይስማሙ ብዙ ቢሆኑም።አልጀዚራ ታድያ በዘገባው እንዲህ ሲል አስፍሯል፣ ‹‹ደጋፊ በሌለበት ባዶ ስታድየም ጎል ማግባት ይጨንቃል። ተጫዋቾችም ስሜታቸውን እንዲገቱ ነው የሚመከሩት››በኢንግሊዝ ፕሪምየር ሊግም ጨዋታዎች በዝግ ስታድየሞች በቅርቡ ይጀመራሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ቡድኖችም ወደ ልምምድ ገብተዋል። እንደውም ከሰሞኑ በወጣው መረጃ መሠረት የዋትፎርድ እና በርንሌይ ቡድኖች ውስጥ ቫይረሱ ያለባቸው ተጫዋቾች ተገኝተዋል።ቢቢሲ እንዳስነበበው ከሆነ አንድ ረዳት አሠልጣኝን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸው በምርመራ ተረጋግጧል። እነዚህ ሰዎች ራሳቸውን አግልለው ለቀናት እንዲቀመጡ ተመክረው በራቸውን ዘግተዋል። በድምሩም በሊጉ 748 ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ከ19 ክለቦች ምርመራ ተደርጎላቸዋል። እንዲያም ሆኖ ለቤተሰባቸው በመስጋት በቤት ውስጥ ልምምዶችን ማድረግን እንመርጣለን ያሉ ተጫዋቾች ጥቂት አይደሉም።ታድያ ይህ መሆኑ ምንአልባት በቅርቡ የሚለውን የሊጉን መጀመሪያ ጊዜ ሊገፋውና ራቅ ሊያደርገው ይችላል እየተባለ ነው።በኢትዮጵያስ?\nጥቂት የማይባሉ የአፍሪካ አገራት የውድድር ዓመቱን በመሰረዝ ስፖርት ጉዳይ አጀንዳ እንዳይሆን አድርገው ቋጭተውታል። በአፍሪካ ደረጃ የሚደረጉ የሻምፕዮን ውድድሮች የሁሉንም የአፍሪካ አገራት ውሳኔ የሚጠብቁ በመሆናቸው፣ እንደ ስምምነቱ አገራት ውሳኔያቸውን አሰምተዋል።ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊጉን ጨምሮ ሁሉንም ውድድሮች ሙሉ ለሙሉ መዝጋቷ የሚታወስ ነው። ይህም ብዙ ውዝግቦችን እያስነሳ ቢሆንም፣ እስከ ውሳኔው ጊዜ ድረስ ከዚህ የተሻለ አማራጭ አልተገኘም። በዚህም ታድያ ብዙ የእግር ኳስ ቡድኖች የሚከስሩ መሆናቸው ግልጽ ነው። በተለይም ከገንዘብ ጋር በተገናኘ የሚኖሩ ኪሳራዎች ቀላል የሚባሉ አይሆኑም።ከዛም ውጪ ውድድሩ ሙሉ ለሙሉ መቋረጡና የዓመቱ አሸናፊ እገሌ ነው አለመባሉ፣ የአፍሪካ ሻምፕዮና የሚካሄድ ከሆነ በሊጉ የነጥብ ሰንጠረዥ ቀዳሚ ላይ ያለው ቡድን ይሄዳል ወይስ ምን ይደረጋል የሚለውም አንዱ መነጋገሪያ ጉዳይ ነበር። በአንጻሩ የግብጽ ፕሪምየር ሊግ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ ሙሉ ለሙሉ የተሰረዘ ቢሆንም፣ የሊጉ ክለቦች በመስማማት በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ መሪነት ላይ የሚገኝ ቡድን በአፍሪካ መድረክ ይወክለናል በማለት ተስማምተዋል።የአገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ከቡድኖቹ ጋር ተወያይቶ አል አህሊና አል ሞካዉሎ የተባሉ ቡድኖች በአፍሪካ ሻምፕዮና፣ ፒራሚድና ዛማሌክ ደግሞ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ ይሳተፋሉ ብለዋል። ይሁን እንጂ የአፍሪካ ሻምፕዮናም ሆነ የኮንፌዴሬሽን ውድድሮች መካሄድ አለመካሄድቸው ላይ ገና የተባለ ነገር የለም።በኢትዮጵያም የእግር ኳስ ቡድን አመራሮች ተመሳሳይ ውይይት ማድረግ ይገባል የሚል አስተያየትን ሲሰጡ ይሰማል። አንዱ ውሳኔ ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮችን ስለሚያስነሳና ብዙ ውሳኔን የሚፈልግ ጉዳይም ስለሚከተል፣ ሰፋ ያለ ውይይት ማስፈለጉ ጥርጥር የለውም። ይህ በእንዲህ እንዳለ ታድያ የሚታየው መደጋገፍም ቀላል የሚባል አይደለም።በቅርቡ የወጣ ዘገባ እንደሚያስረዳው የቡና እግር ኳስ ክለብ አባላት ያልተከፈላቸውን የአንድ ወር ደሞዝ ቡድኑ እንዲይዘውና የኹለተኛውን ወር ደግሞ ግማሹን ብቻ እንዲከፍላቸው መስማማታቸው ይፋ ሆኗል። ከዛም አልፎ ቫይረሱን ለመከላከል በሚደረግ ጥረት የበኩላቸውን በማድረግም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ተስተውሏል።የፌዴሬሽኖች ፈተና\nየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ከስፖርት ኮሚሽን ጋር በመሆን 70ኛውን የፊፋን ስብሰባ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ነበር። ይህም አሁን ባለንበት ግንቦት ወር ይካሄዳል የተባለ ነው። በእርግጥ ይኸው ዓለም ዐቀፍ የእግር ኳስ ጉባኤ በቪዲዮ ሊካሄድ መወሰኑ ከሰሞኑ ተሰምቷል። ይህንንም ፌዴሬሽኑ በይፋዊ ድረ ገፁ ላይ አስፍሮታል።የእግር ኳስ ብቻ ሳይሆን ታድያ አትሌቴክስ ፌዴሬሽንም ቢሆን ለ2020 የቶክዮ ኦሎምፒክ በዝግጅት ዋዜማ ላይ ነበር። ይሁንና ኦሎምፒኩም ቢሆን ለ2021 ተራዝሟል። በ2021 ራሱ የሚካሄደው ቫይረሱ የጠፋ እንደሆነ እንጂ፣ በዚህ ከቀጠለ ውድድሮ ፈጽሞ ሊሰረዝ ይችላል የሚል ግምት ከወዲሁ እየተሰጠ ነው።\nባሕሩ ጥላሁን፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እንዳሉት ከሆነ፣ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ብዙ ነገር ተቀይሯል። ወረርሽኙም የአመራሩን የዓመቱን እቅድ በሙሉ ነው ያዛባው ብለዋል። የሊግ ውድድሮች በጠቅላላ ታግደዋል። ‹‹ወደ መደበኛ የጊዜ ሰሌዳችን መቼ እንደምንመለስ አናውቅም። በጥቂት ሳምንታት ክረምቱም ይገባል። ሌላ መፍትሄ ካልተገኘ በቀር ሊጉን መጨረስ ከባድ ነው›› ሲሉም አስተያየት ሰጥተዋል።እንደ ፌዴሬሽኑ ከሆነ የዓመቱ አሸናፊ ማን እንደሆነ ሳይታወቅ፣ ከየዲቪዝዮኑ አላፊና ወዳቂው ሳይለይ ሊጉን ማቆም የመጀመሪያ አማራጭ መሆን የለበትም ነበር። ይሁንና ከዛ ውጪ አማራጭ የተገኘ አይመስልም።ክለቦች ታድያ ሁኔታው አልቀለላቸውም። ደሞዝ ለመክፈልም እየታገሉ ይገኛሉ። የክለብ ስፖንሰሮችም ቢሆኑ ከገበያ መቀዛቀዝ ጋር ተያይዞ ስምምነት ለመፈራረም ጊዜውን እያራዘሙ በመሆኑ ክለቦች ገንዘብ ማግኛ ምንጫቸው ሁሉ እየነጠፈ ነው። እንዲያም ሆኖ እንደምንም መክፈላቸውን ቀጥለዋል።በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ፌዴሬሽኑ ካለው ላይ ቀንሶ 500 ሺሕ ብር ቫይረሱን ለመከላከል ለሚደረገው እንቅስቃሴ ድጋፍ አድርጓል። ተጫዋቾችም በቤታቸው ውስጥ ሆነውም እንቅስቃሴ ከማድረግ እንዳይቆጠቡ እያሳሰበም ይገኛል።የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ስጋት ደግሞ ከዚህ ይለያል። ኦሎምፒክን ጨምሮ ሁሉም ዓይነት ውድድሮች በጊዜ ተሰርዘዋል። ከፍተኛ የአትሌቲክስ ሕክምና ባለሞያና የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን የጸረ ዶፒንግ ክፍል ተጠሪ ቅድስት ታደሰ እንደሚሉት፣ ይህ መሆኑ አትሌቶቹን እንዲሁም የአትሌቲክስ አገር የሆነችውን ኢትዮጵያን ይጎዳል። በእነዚህ ውድድሮች አለመሳተፋቸውም አትሌቶችን ብዙ እድል ያሳጣቸዋል። እንቅስቃሴያቸውን እንዲሁም ገቢያቸው ጭምር ይጎዳል።ውድድሮች ሰውነታቸውን እንዲጠብቁ ያግዛቸው ነበር የሚሉት ቅድስት፣ እንደ አገርም በዓለም ዐቀፍ መድረክ ልንታይ የምችልበትን እድል ነው ያጣነው ብለዋል። ከዛ የሚብሰው ደግሞ አትሌቶች ለቫይረሱ የበለጠ የመጠቃት እድል ያላቸው መሆኑ ነው።እንደ ዓለማቀፉ የስፖርት ሳይንስ ባለሞያዎች አስተያየት ከሆነ፣ አትሌቶች በውድድርና በከባድ ሥልጠና ውስጥ ከሆኑ ቫይረሱን የመከላከል አቅማቸው ይዳከማል። ቅድስትም በዚህ ላይ ሐሳባቸውን ሲጨምሩ ከመተንፈሻ አካል ጋር ለሚገናኝ በሽታ ተጋላጭ መሆናቸውን ነው ያነሱት። ‹‹አትሌቶቻችን በሩጫ ጽናታቸው ይታወቃሉ። ይህም የመተንፈስ አቅማቸውን እስከ ጥግ እንዲጠቀሙበት የሚያደርግ ነው። በዚህ ምክንያት ነው ቫይረሱ ምን ያህል ሊያጠቃቸው እንደሚችል መረዳት ያለባቸው›› ብለዋል።የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ታድያ ያለውን የአትሌቶች ትግል እንዲሁም ያለባቸውን ፈተና በመመልከት ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ የሥልጠና ቡድን አባላት፣ 4 ሚሊዮን ብር እና አስፈላጊ የተባሉ የሥልጠና ቅሳቁሶችን አሰራጭቷል። ‹‹ሁሉም 211 ብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድኖችና 56 አሠልጣኖች እያንዳንዳቸው 15 ሺሕ ብር ይከፈላሉ። ይህም ለማበረታቻና ባሉበት ጸንተው ራሳቸውንም እየጠበቁ እንዲቆዩ ነው ለማገዛ ነው።›› ብሏል፣ ፌዴሬሽኑ ባወጣው መግለጫ።ከአዲስ ማለዳ እህት መጽሔት ኢትዮጵያን ቢዝነስ ሪቪው በዐቢይ ወንድይፍራው የተጻፈውን መነሻ በማድረግ ፣ ወቅታዊ ተጨማሪ መረጃዎች ታክለውበት የተዘጋጀቅጽ 2 ቁጥር 81 ግንቦት 15 2012", "passage_id": "a502a9474a8e89c64e46e76599f85f27" } ]
13133d5e11f3a88925fcaf1fe0c5fbea
5cb36a0cd9913e44800f30f6ed4ff301
የስፖርቱ በቫይረሱ ሳቢያ ብዙ ተጽዕኖ እያስተናገደ ነው
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ያስቻለ ፈውስ በዓለም ሳይንቲስቶች፣ የህክምና ጠቢባንም ይሁን በሀያላን አገራት አቅም ማምጣት አልተቻለም። ይህም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ከመለወጥ አንስቶ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በርካታ አሉታዊ ተፅዕኖው እንዲያርፍ አድርጓል። የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ተጽዕኖ እያስተናገደ ከመሆኑ ባሻገር፤ ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጉን መረጃዎች ያመላክታሉ። የስፖርት ቤተሰቡ በቫይረሱ ስርጭት ስጋት የዓለም ታላላቅ የስፖርት መድረኮች ተቆልፈውበት ሁነኛ የመዝናኛ አማራጩን አጥቶ በየቤቱ ቆዝሟል። የስፖርቱ ዓለም ታላላቅ ከዋክብትም ረብጣ ገንዘብና ዝናቸው ከደጃቸው እንዲወጡ አቅም አልሆናቸውም። የቫይረሱን አደጋ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም፤ ለመከላከል የሚደረገው ርብርብ በተጠናከረ መልኩ እንደቀጠለ ነው። የአለም ህዝብ እያሸበረ ያለውን ተህዋሲ ለመቆጣጠርና ለመከላከል በሚደረገው እንቅስቃሴ በስፖርቱ ማህበረሰብ በኩል እየተደረገ ያለው ተሳትፎ ትልቅ ስፍራ ይወስዳል። በተለያዩ ሀገራት በከፍተኛ ፍጥነት የዓለምን ክፍል እያዳረሰ የሚገኘው ቫይረስ ለመቆጣጠርና አደጋ ለመቀነስ በሚደረግ እንቅስቃሴ ላይ የስፖርት ማህበራት፣ የስፖርቱ ቤተሰብ፣ ተጫዋቾች ትልቅ ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ በተመሳሳይ ኮሮና ቫይረስ የቅድመ መከላከል ተግባራትን በመደገፍና በመሳተፍ ትልቅ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን ለመታዘብ ተችሏል። የአዲስ አበባ ከተማ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚደረገውን እንቅስቃሴ መሰረት በተለየ መልኩ ህዝብን አሳታፊ የሆነ የቅድመ መከላከል ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። በምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በመዲናዋ የኮሮና ቫይረስን ቅድመ ጥንቃቄና መከላከል አስመልክቶ የተደረገው የድጋፍ ማሠባሰብ ጥሪ የዚሁ አካል ተደርጎ የሚጠቀስ ይሆናል። በምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ጥሪ ከተደረገ ጀምሮ የተጠናከረ ድጋፍ በከተማዋ በተለያዩ አቅጣጫዎች እየተደረገ ባለው ተሳትፎ ውስጥ የስፖርት ማህበረሰብ ተሳትፎ አንጸባራቂ እንደነበር መታዘብ ተችሏል። የስፖርቱ አንዱ ባህሪና መገለጫው በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳታፊ በማድርግ ኃላፊነት መወጣት እንደሆነ ይታመናል። የስፖርት ቤተሰቡ ይሄንኑ መርህ መሰረት በማድረግ ለከንቲባው ጥሪ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ህዝባዊነታቸውን እያረጋገጡ ካሉት አካላት መካከል በፊት አውራሪነት ይቀመጣል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሎም በመዲናችን የስፖርት ቤተሰቡ ተሳትፎ ገና ከጅምሩ አበረታች የሆነ መንገድ ያሳየ ሲሆን፤ እውቅ ስፖርተኞችና የስፖርት ማህበራት የነበራቸው ድጋፍ ተሳትፎ ለዚህ ምስክር ይሆናሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የእግር ኳስ ደጋፊዎች ማህበር አባላት መጋቢት 26 ቀን 2012 ዓ.ም የጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ይሄንኑ ያመላክታል። የማህበሩ አባላት በኩል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመዲናዋ ሊያጋጥም የሚችለውን አደጋ ለመከላከል እያደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ የሚያስችል ስራ ለመስራት ከስምምነት ተደርሷል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የእግር ኳስ ደጋፊዎች ማህበር አባላት ይሄንኑ መሰረት በማድረግ «ወገን ለወገን ደራሽ ነው» የሚል መሪ ቃልን በማንገብ መጋቢት 26 ቀን 2012 ዓ.ም ወደ ስራ ተገብቷል። ማህበሩ ከህብረተሰብና ከተለያዩ ለጋሾች የምግብ፣ የቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፍ በማሰባሰብ ህዝባዊነቱን የሚያሳይ ይሆናል። በዚህ ታላቅ ፕሮግራም ላይ በመገኘት አርዓያነቱ እንዲጠናከርና ተግባሩ እንዲቀጥል የተጋረጠውን ቫይረስ ለመግታት፣ ህብረትንና አንድነትን ለማሳየት፣ ወሳኝነቱን በመግለፅና ለማበረታታት በርካቶች የታሪኩ አካል በመሆን እየተንቀሳቀሱ ይገኛል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብርሀቱ እና የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ቢኒያም ምሩፅ ይፍጠር ደግሞ ፊት አውራሪ በመሆን ተግባሩን እየመሩ ህዝባዊነታቸውን ያሳዩ መሆናቸው ታውቋል። በማህበሩ በኩል በሚደረገው እንቅስቃሴ በርካታ የስፖርት ቤተሰቦች ለዚህ አላማ እጃቸውን እየዘረጉ የወገን አሌንታነታቸውን እያሳዩም ይገኛሉ። ለዚህም እንደ ማሳያ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግበሩ ለማጠናቀቅ የተያዘው ቀን ማክሰኞ ቢሆንም የተሳትፎው ከፍተኛ መሆን ወደ ረቡዕ መሸጋገሩ እንደ ማሳያ ይጠቀሳል። የማህበሩ አባላት አንዱ የሆነችው አሰልጣኝ ሰላም ዘርአይ፤ ቀደም ብሎ እስከ ሰኞ ድረስ ይጠናቀቃል በሚል ተይዞ የነበረው ቀነ ገደብ በመላ ሀገሪቱ ያሉ አሰልጣኞች የሚሰጡት ምላሽ እየጨመረ መጥቷል። በዚህ መሰረት መዋጮውን ለማሰባሰብ ተጨማሪ ጊዜ እንዲኖር በመጣው ጥያቄ መሰረት እስከ ረቡዕ ስምንት ሰዓት ድረስ ሊራዘም ችሏል። ‹‹በመሆኑ አሰልጣኞች ቀደም ሲል በተጠቀሰው የባንክ ቁጥር አቅማችን የፈቀደውን እንድናደርግ ከአክብሮት ጋር እንጠይቃለን›› ስትል አሰልጣኝ ሰላ በፌስቡክ ገጿ አሳውቃለች። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የእግር ኳስ ደጋፊዎች ማህበር አባላት በዚህ መሰረት የገንዘብ፣ የአይነትና የቁሳቁሶች ድጋፍ እስከ ረቡዕ ከተካሄደ በኃላ በሚወጣ ፕሮግራም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በተገኙበት ያስረክባሉ ተብሏል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የእግር ኳስ ደጋፊዎች ማህበር አባላት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ከመጋቢት 26 እስከ መጋቢት 30 ቀን 2012 ዓ.ም የሚዘልቅ ይሆናል። አዲስ ዘመን መጋቢት 29/2012ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29948
[ { "passage": "ቦጋለ አበበ ጃፓን ከሰባት ዓመታት በላይ ብዙ የለፋችበት የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝግጅት ካለፈው ዓመት ጀምሮ የዓለም ሕዝብ የጤና ጠንቅ በሆነው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሞ ዘንድሮ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለታል። ኦሊምፒኩ በተራዘመው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንደሚካሄድም እርግጠኛ ሆነው የውድድሩ አዘጋጆች መናገር ከጀመሩ ሰነባብተዋል። የተለያዩ አገራትም በአዘጋጆቹ ተማምነው የስፖርት ልዑካን ቡድኖቻቸውን እያዘጋጁ ይገኛሉ።የዓለም አቀፉን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጨምሮ የውድድሩ አዘጋጆች አሁንም ድረስ ውድድሩ እንደሚካሄድ እርግጠኛ የሆኑት ወረርሽኙ ኦሊምፒኩ እስኪቃረብ አንድ መፍትሄ ያገኛል በሚልና በሙከራ ላይ የሚገኙትን የተለያዩ ክትባቶች ተማምነው ነው። ያም ሆኖ ሰሞኑን እየወጡ የሚገኙ መረጃዎች ወረርሽኙ እየቀነሰ ከመሄድ ይልቅ በፍጥነት እየተስፋፋ እንደሚገኝ ያመላክታሉ። ጃፓን ውድድሩን በምታካሂድበት ወቅት ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ከአገሪቱ ዜጎች በበለጠ ብዙ ቁጥር ያላቸው እንግዶች ስጋት ሊሆኑ እንደሚችሉ የገመተች ቢሆንም፣ በተቃራኒው ራሷ ጃፓን የእንግዶቿ ስጋት ልትሆን እንደምትችል በቅርብ የወጡ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው።ወረርሽኙ ለዓለም ስጋት ከሆነ ወዲህ ኦሊምፒኩን በዋናነት የምታስተናግደው ከተማ ቶኪዮ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ወር ውስጥ ብቻ በቫይረሱ የተጠቁ አስር ሺህ ሰዎች የተገኙባት ሆናለች። ይህም በቀጣዩ ክረምት በሚካሄዱት የኦሊምፒክና የፓራሊምፒክ ውድድሮች ላይ ዳግም ተመሳሳይ ስጋት እንዲፈጠር ያደረገ ሲሆን በብዙዎች ዘንድ ጥያቄ እየተነሳበት ይገኛል።ኦሊምፒኩ ሊካሄድ ስድስት ወራት በቀሩበት በዚህ ወቅት ባለፈው ሐሙስ ብቻ ቶኪዮ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ስምንት መቶ ሃያ ሁለት ሰዎች በቫይረሱ የተያዙባት ከተማ ሆናለች። ይህም ወረርሽኙ በሀገሪቱ ከተከሰተበት ወቅት ወዲህ የታየ ከፍተኛው ቁጥር ሆኖ ተመዝግቧል። የቶኪዮ ከተማ አስተዳዳሪ ዩሪኮ ኮኢኬ ከጃፓን ታይምስ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስም የቶኪዮ የጤና ተቋማት ከአቅማቸው በላይ ሕመምተኞችን እያስተናገዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ‹‹ሆስፒታሎች ተዘግተዋል፣ በዚህ ወሳኝ ወቅት በቅርቡ መሰረታዊ አገልግሎት መስጠት ሊያቆሙም ይችላሉ›› በማለትም በከተማዋ ያለውን ሁኔታ ገልፀዋል።ቶኪዮ ወረርሽኙ ከተከሰተ ወዲህ እስካለፈው ሳምንት መጨረሻ ብቻ ሃምሳ ሁለት ሺህ ሰዎች በቫይረሱ የተጠቁባት ከተማ ስትሆን አምስት መቶ ያህል ሰዎችም ሕይወታቸው አልፏል። በአጠቃላይ በጃፓን ደግሞ እስካፈው ሰኞ ድረስ በአማካይ ከሁለት ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ እየተጠቁ እንደሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፤ እስካሁን ከሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ በላይ ሰዎች በቫይረሱ መሞታቸው ታውቋል።የቶኪዮ ተላላፊ በሽታዎች መቆጣጠሪያ ማዕከል ዳይሬክተር ኖሮዪ ኦማጋሪ በበኩላቸው ‹‹የቫይረሱ ሥርጭት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፣ ከዚህ የበለጠ ብዙ ሰዎች በቫይረሱ እንዳይጠቁ ጠንካራ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው›› በማለት ለአገሪቱ ጋዜጣ ተናግረዋል።ጥቂት ቀናት በቀሩት የፈረንጆቹ አዲስ ዓመትና የገና በዓል አከባበር ወቅት በርካታ የአውሮፓ አገራት የወረርሽኙን ሥርጭት ለመቀነስ ጠንካራ መመሪያዎችን ከማውጣት ባሻገር በአገር አቀፍ ደረጃ እንቅስቃሴዎችን እስከ መግታት ደርሰዋል። ይህን በመመልከትም ጃፓን በአንፃራዊነት የተሻለ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ የሚናገሩ አሉ። ከቀናት በፊት የእንግሊዝ መንግሥት የጤና ቢሮ ሃላፊ ክሪስ ዊቲይ በአይነቱ ልዩ የሆነና በፍጥነት የመዛመት ባህሪ ያለው የኮቪድ-19 ቫይረስ በአገሪቱ እንደተገኘ ለዓለም ጤና ድርጅት ጭምር በማሳወቅ ጥንቃቄ እንዲደረግ ማሳሰቡ ይታወቃል። በአገሪቱ የቫይረሱ ሥርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱም ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በአዲስ ዓመትና በገና በዓል ዋዜማዎች ወቅት በሚደረጉ መዝናኛዎች ላይ ጠንካራ እግድ አስቀምጠዋል። መዲናዋ ለንደንን ጨምሮ ቫይረሱ በስፋት በተሰራጨባቸው የደቡብ እንግሊዝ ከተሞችም ጠንካራ የተባሉ ገደቦች ተጥለዋል።አስቀድሞ በቫይረሱ ከፉኛ የተጠቃችው ጣሊያንን ጨምሮ ኔዘርላንድስና ጀርመን እስከ አዲሱ ዓመት ድረስ ማንም ከቤቱ እንዳይወጣ እግድ አስቀምጠዋል። አውስትራሊያም ከገና በዓል በኋላ ተመሳሳይ እርምጃ እንደምትወስድ መረጃዎች ጠቁመዋል። በቅርቡ በቤልጂየም ብራሰልስ የተካሄደውን የአውሮፓ ሕብረት ስብሰባ ከተካፈሉ በኋላ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑዔል ማክሮንና የስሎቫኪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኢጎር ማቶቪች እንዲሁም ሌሎች የአገር መሪዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ይታወቃል። ባለፈው ዓመት በቫይረሱ ሥርጭት ስጋት የገባቸው የኦሊምፒክ አዘጋጆች ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ታላቁን የስፖርት መድረክ ለማራዘም መገደዳቸው ይታወቃል። በዚህም የተነሳ አዘጋጅ ኮሚቴው ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ከወር በፊት አሳውቋል። ወረርሽኙ ዳግም በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱን ተከትሎም የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ላይ ጥያቄ ተነስቷል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽን ጨምሮ የተለያዩ ሃላፊዎች ግን አሁንም ውድድሩን በጥንቃቄ ለማካሄድ ሃሳብ አለወጡም።ቶኪዮ በኦሊምፒኩ ወቅት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በምትወስደው እርምጃ ከዘጠኝ መቶ ስልሳ ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ እንደምታደርግ የተዘገበ ሲሆን፣ የውድድሩ አዘጋጆች ቫይረሱን ለመዋጋት ከአገሪቱ መንግሥት ጋር በየጊዜው ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶችና የስፖርት ልዑካን ቡድኖች የፊት ጭምብል ማጥለቅና ርቀትን መጠበቅ እንደሚገባቸው አዘጋጆቹ በቅርቡ ጠቁመዋል፤ ከውድድሩ በኋላ በጃፓን የሚቆዩበት ጊዜ አጭር እንደሚሆንም አሳውቀዋል።እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ቻይናና ሩሲያን የመሳሰሉ የተለያዩ አገራት ለወረርሽኙ መፍትሄ ይሆን ዘንድ የተለያዩ ክትባቶችን በማምረት የተሳካ ሙከራ እንዳደረጉ መናገር ከጀመሩ ሰንብተዋል። ክትባቱ በምን አይነት ፍጥነት ለዓለም ሕዝብ ተዳርሶ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ከስጋት ነፃ በሆነ መልኩ ይካሄዳል የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው። በኦሊምፒኩ ለመሳተፍ ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ ከቫይረሱ ነፃ የሆኑ አትሌቶች ክትባቱን ለማግኘት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል አይሰጣቸውም የሚሉ ጥያቄዎችም ከወዲሁ እየተነሱ ይገኛሉ።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ባለፈው ወር በጃፓን ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የተሳካ የኮቪድ-19 ክትባት ተገኘ መባሉን ተከትሎ እንኳን ስፖርተኞች የስፖርቱ አፍቃሪዎች ስቴድየም ገብተው የኦሊምፒክ ውድድሩን ካለ ስጋት እንደሚመለከቱ እርግጠኛ ሆነው ሲናገሩ ተደምጠዋል።የጃፓን መንግሥትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አትሌቶች የወረርሽኙን ክትባት እንዲያገኙ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረጉ ይገኛሉ። ከዚህ ባሻገር በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶችና የስፖርት ቤተሰቦች ወረርሽኙን ለመከላከል የተለያዩ ጥብቅ መመሪያዎችን ማክበር እንደሚገባቸው ቀደም ሲል አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።ባለፈው ዓመት ወረርሽኙ በኦሊምፒኩ አዘጋጅ ጃፓንም ይሁን በሌሎች አገራት እንዲህ እንዳሁኑ ባልጠነከረበት ወቅት ለመራዘም የተገደደውን ይህን ውድድር፣ ዘንድሮ ወረርሽኙ ‹‹ክትባት ተገኝቶለታል›› እየተባለም መልኩን እየቀያየረ የብዙዎች ስጋት በሆነበት ጊዜ እንዲካሄድ መወሰን ለብዙዎች አልተዋጠም። ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴውም ይሁን የጃፓን መንግሥት ውድድሩን ለማካሄድ እርግጠኛ ሆነው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙትም ኦሊምፒኩ ካልተካሄደ የሚደርስባቸውን ትልቅ ኪሳራ በማስላት ሊሆን እንደሚችል ትችቶች ይሰነዘራሉ።ኦሊምፒኩ ባለፈው ዓመት መካሄድ ሲገባው ወደ ዘንድሮ በመራዘሙ ብቻ ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ዶላር ኪሳራ እንዳደረሰ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ይህን ኪሳራ ለመሸፈን የቶኪዮ ከተማ አንድ ነጥብ አንድ ቢሊየን ዶላር ወጪ እንዳደረገ ተዘግቧል፤ የውድድር አዘጋጅ ኮሚቴው አንድ ቢሊየን ዶላር ወጪ አድርጓል። ቀሪውን ሰባት መቶ ሚሊየን ዶላር ደግሞ የጃፓን መንግሥት እንደሚሸፍን ታውቋል። ኦሊምፒኩ ከመራዘሙ አስቀድሞ አስራ ሦስት ቢሊየን ዶላር ወጪ እንደሚጠይቅ ተገልጿል።በዘንድሮው ዓመት ሳይካሄድ ከተራዘመ ወይም ከተሰረዘ ቀድሞ ከተያዘለት በጀት እስከ አራት እጥፍ ኪሳራ ሊያደርስ እንደሚችል መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013", "passage_id": "1dd6701861055b016f1ec03cf6a04fb5" }, { "passage": "የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከኦሊምፒክ ቀድሞ ይካሄዳል የኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) በዓለም ላይ በከፍተኛ ፍጥነት መሰራጨቱን ተከትሎ የሁሉም ዓለም አቀፍ የስፖርት መርሃግብሮች ዝብርቅርቅ መውጣቱ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በርካታ ታላላቅ የስፖርት መርሃግብሮችን ዳግም መከለስ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በዚህም መሰረት ክለሳ የተደረገባቸው የተለያዩ መርሃግብሮች ውዝግብ ሲያስነሱ ማየት እየተለመደ መጥቷል፡፡ \nከተያዘለት መርሃግብር እንዲራዘም የተደረገው የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ2021 እንዲካሄድ ከተራዘመው የቶኪዮ ኦሊምፒክ አስቀድሞ እንዲካሄድ የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ውሳኔ ላይ መድረሱን ከሁለት ቀናት በፊት አሳውቋል፡፡ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሐማድ ካልካባ በአልጄሪያ የሚካሄደው የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከቶኪዮ ኦሊምፒክ ከአንድ ወር ቀደም ብሎ እንደሚካሄድ ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ የዓለም አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት ካልካባ የውድድሩ አዘጋጅ አገርም አዲሱን መርሃግብር የመቀበል ግዴታ እንዳለባት ገልፀዋል፡፡ \nካልካባ ቻምፒዮናው ከተራዘመው ኦሊምፒክ በፊት መካሄዱ ለአትሌቶች ጥቅም እንደሚኖረው የገለፁ ሲሆን ውድድሩ በተከለሰው የኦሊምፒክ ማጣሪያ መርሃግብር ውስጥ እንደሚካተት ጠቁመዋል፡፡ ‹‹ውድድሩ የኦሊምፒክ ማጣሪያ(ሚኒማ) ለሚፈልጉ አትሌቶች ጠቃሚ ይሆናል›› ያሉት ካልካባ የዓለም አትሌቲክስ የኦሊምፒክ ማጣሪያ መርሃግብር እስከ ቀጣዩ ዓመት ሰኔ ወር እንዲራዘም ግፊት ማድረጉን አስታውሰዋል፡፡ \nበኮሮና ቫይረስ ስጋት የተነሳ የአትሌቲክስ ስፖርት የኦሊምፒክ ማጣሪያ ውድድሮች እስከ መጪው ታህሳስ ወር ድረስ እንዳይካሄዱ የዓለም አትሌቲክስ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ እስከ ተጠቀሰው ጊዜ የሚካሄዱ ማንኛቸውም ውድድሮችና ውጤቶች የኦሊምፒክ ማጣሪያም ይሁን እውቅና እንደማያገኙ ማስጠንቀቁ ይታወሳል፡፡ ይህ የዓለም አትሌቲክስ ውሳኔ በበርካታ ታላላቅ የዓለማችን አትሌቶች የሰላ ትችት ሲሰነዘርበት እንደሰነበተ ይታወቃል፡፡ \nበኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት የስፖርቱ ዓለም ካለፉት ሁለት ወራት በላይ እንቅስቃሴው ተገድቦ ቢቆይም ከቅርብ ቀናት ወዲህ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ለመመለስ ሲፍጨረጨሩ እየተስተዋለ ነው፡፡ ታላላቆቹን አውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች ጨምሮ አንዳንድ አገራትም ስፖርታዊ ውድድሮቻቸውን ለማስጀመር ከቫይረሱ ስጋት ነፃ ሳይሆኑ ጥረት እያደረጉ ሲሆን አብዛኞቹ ውድድሮችን በዝግ ስቴድየሞች በማድረግ የውድድር ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት መርሃግብሮቻቸውን ስለመፈፀም እየተጨነቁ ይገኛሉ፡፡ \nበርካቶቹ የዓለም አቀፍ ውድድሮች ግን ቀደም ሲል ቫይረሱ በቀጣዩ ዓመት ይጠፋል ወይም በቁጥጥር ስር ይውላል በሚል ተስፋ ወደ ቀጣይ ዓመት እንዲዞሩ መወሰናቸው ይታወሳል፡፡ ከነዚህ መካከል በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዘግይቶም ቢሆን በቫይረሱ ስርጭት ስጋት የተነሳ ታላቁን የስፖርት መድረክ ለአስራ ስድስት ወራት እንዲራዘም ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህም እንደሌሎቹ ውድድሮች ሁሉ ቫይረሱ በቀጣዩ ዓመት በቁጥጥር ስር ይውላል ከሚል ተስፋ እንጂ በተጨባጭ መረጃና ማስረጃ አልነበረም፡፡ በርካቶቹ ይህን ተስፋ የሙጥኝ ብለው እያንዳንዱ ቀን እንደ ዓመት እየረዘመባቸውም ቢሆን ቀጣዩን ዓመት በጉጉት እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡ \nየቫይረሱ ስርጭት ግን በተቃራኒው እየቀነሰ ከመሄድ ይልቅ በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል፡፡ ይህንን ያስተዋሉ የጤና ባለሙያዎችም ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በቀጣዩ ዓመት ላይካሄድ እንደሚችል ከወዲሁ እየተናገሩ ይገኛሉ፡፡ የኦሊምፒኩ አዘጋጅ የሆነችው ጃፓን የተላላፊ በሽታዎች ፕሮፌሰር የሆኑት ኬንታሮ ዋታ የቫይረሱ ስርጭት ኦሊምፒኩ በተራዘመበት ወቅት በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ አጠራጣሪ በመሆኑ ውድድሩ ላይካሄድ እንደሚችል ስጋታቸውን ለመገናኛ ብዙሃን መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ \nበዓለም ላይ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ከተስፋ በስተቀር የቫይረሱ ስርጭት በጊዜ የሚገታ ወይም ፈውስና ክትባት በዚህ ጊዜ እውን ይሆናል የሚያስብል እንዳልሆነ መታዘብ ይቻላል፡፡ ይህንን ከግምት ያስገቡት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ኦሊምፒኩ የቫይረሱን ስጋት ለማምለጥ በአስራ ስድስት ወራት ቢራዘምም ከቫይረሱ ተፅዕኖ ሊያመልጥ እንደማይችል ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ማመልከታቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ማስነበቡ ይታወሳል፡፡ የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮናም ከዚህ የተለየ እድል እንደማይገጥመው ማንም እርግጠኛ አይደለም፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 8/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "d9a6c910e351136919c0b9932f8b36b6" }, { "passage": "የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የዓለምን ስፖርት ቁመና ወዳልታሰበ አቅጣጫ የወሰደ ስለመሆኑ እየተነገረ ይገኛል።የስፖርት እንቅስቃሴ ወረርሽኙን መከሰት ተከትሎ መታገዳቸው በስፖርቱ ሊገኙ የሚችሉ በቢሊዮን የሚቆጠር ገቢ ያሳጣው ስለመሆኑ መረጃዎች ያመላክታሉ።ይሄንኑ ዋቢ በማድረግ ወረርሽኙ ስፖርቱን ጥልቅ ወደሆነ የፋይናንስ ቀውስ የዳረገው ስለመሆኑ መናገር ያስችላል።በዘርፍ አዋቂዎች በተደረጉም ጥናቶች«ኮቪድ -19 በስፖርቱ ላይ ያደረሰው ከፍተኛ የሆነ የፋይናንስ ቀውስ መዘዙ ዛሬ ላይ የሚቆም ሳይሆን እስከ ቀጣዮቹ 10 ዓመታት የሚሻገር ይሆናል »የሚሉ መሆናቸውን ልብ ይሏል።የስፖርቱ መስክ በወረርሽኙ ምክንያት ከፍተኛ መቃወስን ያስተናግድ እንጂ ፤ወረርሽኙን ለመዋጋት ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ረገድ ግንባር ቀደሙ እንደነበር ታዝበናል።በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የስፖርት ማህበረሰቡ ወረርሽኙን ለመዋጋት ከነጉዳቱ ትልቅ መስዋዕትነት በማድረግ ለሰብዐዊነት ሰፊ ቦታ የሚሰጥ ማህበራዊ ክዋኔ መሆኑን አስመስክሯል። በሀገራችን በተመሳሳይ የስፖርት ቤተሰቡ በዘመነ ኮሮና ሰብዐዊነትን መሰረት ያደረጉ ተግባራትን በማከናወን ይሄንኑ አስመስክሯል።በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት ፣የስፖርት ማህበራት፣ተጫዋቾች ፣አትሌቶች፣የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል በሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በስፖርት ማህበረሰቡ በኩል ሰብዐዊነትን መሰረት አድርጎ ህዝባዊነትን በመታጠቅ «ወገን ለወገን »ደራሽነቱን በገንዘብና በቁሳቁስ አሳይቷል።በተለይም በክለቦችና በተጫዋቾች በኩል ወረርሽኙን ለመዋጋት ያሳዩትን ቀናኢነት የሚቃረን ተግባር በአንዳንድ ክለቦች እየተፈፀመ ስለመሆኑ መረጃዎች መውጣት ከጀመሩ ውለው አድረዋል። በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ድጋፍ ለሚገባቸው የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች በሚሊዮን ገንዘብ ማበርከታቸውን ሲናገሩ የከረሙ ክለብ ተጫዋቾች «የደመወዝ ያለህ» ሲሉ ቅሬታቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊጉ የሚጫወቱ የተለያዩ ክለብ ተጫዋቾች «ክለቦች ደሞዝ ከለከሉን »ከሚሉት ቅሬታዎች ጀርባ የስፖርት ቤተሰቡ ከገነባው በጎ መልክ ጋር የማይጣጣም እንደሆነ በርካቶች ትችት ሰንዝረዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከደመወዝ ክፍያ ጋር ተያይዞ በክለቦችና በተጫዋቾች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት፣ ክለቦች በገቡት የውል ስምምነት መሠረት የተጫዋቾቻቸውን ወርኃዊ ክፍያ እንዲከፍሉ ያስተላለፈው ተደጋጋሚ መመርያና ማስጠንቀቂያ መፍትሔ ሊሆን እንዳልቻለ የሚናገሩ አሉ፡፡በብሄራዊ ፌዴሬሽኑን መመሪያ መሰረት መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ ማግኘት ካልቻሉ መካከል የሰበታ ከተማ ተጫዋቾች ይገኛሉ።ከሕግና ሥርዓት ውጭ ሆኖ የቆየው የክለቦች የፋይናንስ አሠራር በተለይም ከተጫዋቾች ክፍያ ጋር ተያይዞ እየተነገረ ያለው ጉዳይ ለእግር ኳሱ ተጨማሪ ውድቀት እንዳይሆን የተጫዋቾች ብቻም ሳይሆኑ የክለብ አሠልጣኞች ጭምር ሥጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ ፡፡ከእነዚህ አሰልጣኞች መካከል የችግሩ ባለቤት ከሆኑት መካከል ከሚጠቀሰው የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ከለብን በማሠልጠን ላይ የሚገኘው አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ይገኙበታል ፡፡ አሠልጣኙ የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብን ለማሠልጠን ሲስማሙ ለተጫዋቾች ሊከፈል የሚገባውን ወርኃዊ ክፍያ ጨምሮ በሚያቀርቡት ዕቅድ መሠረት እንዲፈጸም ከክለቡ ጋር ስምምነት እንደነበረው፣ ሆኖም ሥራ ከጀመረበት ዕለት አንስቶ እስካሁን በስምምነቱ መሠረት ሁኔታዎቹ ተፈጻሚ እየሆኑ እንዳልሆነ ያስረዳል፡፡በፕሪሚየር ሊጉ የተለያዩ\nክለቦችን በማሠልጠን የሚታወቀው አሠልጣኝ ውበቱ አባተ የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብን ለማሠልጠን ሲስማማ፣ በዕቅድ ደረጃ የተያዙ በተለይም ክፍያን ጨምሮ የተጫዋቾች አያያዝ፣ ለቅድመ ዝግጅት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችና መሰል ጉዳዮች እንደሚሟሉ ቃል የተገባለት ስለመሆኑ ጭምር ያስረዳል፡፡አሠልጣኙ፣ «ስምምነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በክለቡ ሥራ ሲጀምር ሁለት ዓይነት ማልያና ቁምጣ እንዲሁም ተጫዋቾች በልምምድ ጊዜ የሚለብሱትን መለያ፣ ኮኖዎችን፣ የልምምድ ኳሶችንና ሌሎችም ቁሳቁሶች (ቆይቶ ቢሟሉም) በወቅቱ ግን በግሌ ገዝቼ ነው፡፡ በዚያ ላይ ወደ ክለቡ እንደመጣሁ ያስፈረምኳቸውን ጨምሮ ለሌሎችም ተጫዋቾች የሐምሌ፣ የነሐሴና የመስከረም ወር ክፍያ የተከፈለው ከሦስት ወር በኋላ ነው፡፡ በቅርቡ ወደ ሆነው ስንመጣ ደግሞ የግንቦትና የሰኔ ወር ክፍያ እስካሁን አልተከፈለም፤» ሲል ያስረዳል፡፡በአሁኑ ወቅት ምንም እንኳ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጉዳይ ገና መፍትሔ ባያገኝም፣ ለቅድመ ዝግጅት የሚያስፈልጉ አንዳንድ ጉዳዮች ቀደም ሲል እንደነበረው ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር ለክለቡ አመራሮች ያለፈውን ዓመት ሪፖርት ጨምሮ በቀጣይ ሊሟሉ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ጥያቄ ማቅረቡን ጭምር አሠልጣኙ አልሸሸገም፡፡ምክንያቱን አስመልክቶ አሠልጣኝ ውበቱ፣ «ካለፈው አንድ ዓመት ተሞክሯችን መረዳት የምንችለው በዚህ ሁኔታ ውጤት ከማምጣት ጀምሮ በፕሪሚየር ሊጉ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ለመቀጠል ከባድ ነው፡፡ በዚህ ዓይነት አካሄድና አሠራር አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ክለቡ ለማምጣት ይቸግረኛል፡፡ ምክንያቱም የክለቡ አሠልጣኝ እንደመሆኔ ተጫዋቾች እንዲሟላላቸው የሚጠይቁትን ጥያቄ የማላስፈጽም ከሆነ በእኔ ላይ እምነት ስለሚያጡ፣ በሁለታችን መካከል የሚኖረው ግንኙነት መልካም ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ ማለት በተጫዋቾች ዘንድ ሊኖረኝ የሚገባው ክብር በራሱ ዋጋ እንዳይኖረው የሚያደርግ ነው»ይላል፡፡ ወቅቱ ክለቦች ለ2013 የውድድር ዓመት ዕድሜ ዝግጅት የሚያደርጉበት መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ ክለቦች የሚፈልጓቸውን ተጫዋቾች የሚያዘዋውሩበት ነው:: ከተጫዋቾች ክፍያ ጋር ተያይዞ ችግር የሌለባቸው አንዳንድ ክለቦች ኮንትራት ያጠናቀቁ ተጫዋቾቻቸውን ጨምሮ ሌሎችን ተጫዋቾች እያስፈረሙ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብ አሠልጣኝ ውበቱ እንደሚናገረው ከሆነ፣ ክለቡ የተጫዋቾች ክፍያን ጨምሮ በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ይገኛል:: ሰበታ ከተማ የፊርማን ጨምሮ ወርኃዊ ክፍያን ያጓደለበት ምንም እንደሌለ የሚናገረው አሠልጣኝ ውበቱ አባተ፤«ይህ ለእኔ ምንም ዓይነት እርካታ አይሰጠኝም፣ ምክንያቱም በወርሃዊ ክፍያና በሌሎችም ጥቅማ ጥቅሞች ያኮረፈ ተጫዋች ይዤ የትም መድረስ እንደማልችል ስለምረዳ ነው፤»ሲል የእርሱ ፍላጎት መሟላት የተጫዋቾችን በደል ቸል ብሎ ማለፍ እንደከበደው ያስረዳል ።በሰበታ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች እያሰሙት እንዳለው የደሞዝ ጥያቄ ሁሉ በፕሪሚየር ሊጉ የሚጫወቱ በርካታ ክለቦች ለተጫዋቾቻቸው ደሞዝ ባለመክፈላቸው ተጫዋቾች ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ መዳረጋቸውን መሰማቱ ችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል ።ከእነዚህ መካከል የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ የሚጠቀስ ሲሆን የክለቡ ተጫዋቾች «በኮሮና ቫይረስ ውድድሮች ከተቋረጡ ጀምሮ የሦስት ወር ደሞዛችን አልተከፈለንም »ሲሉ በክለቡ ላይ ቅሬታቸውን ማሰማታቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነበር።ከተጫዋቾች የደመወዝ ቅሬታ ጋር ተያይዞ እየታየ ላለው ሰፊ ችግር የወልዋሎ አዲግራት እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች ተጨማሪ ማሳያ ይሆናሉ።የወልዋሎ አዲግራት እግር ኳስ በተለይ የሀገር ውስጥ ተጫዋቾች ክለቡ «የ4 ወር ደሞዝ ስላልተከፈለን ከነ ቤተሰባችን ለከፍትኛ ችግር ተዳርገናል »ሲሉ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ ነበር ።ክለቡን በፕሪሚየር ሊጉ የተሳትፎ ባለቤት እንዲሆን ማድርጋቸውን አስታውሰው ፤በክፋው ቀን ግን ከጎናቸው ሊሆን አለመቻሉ ትልቅ የሞራል ጉዳት እንዳደረሰባቸው ተናግረዋል።ከወርኃዊ ክፍያ ጋር ተያይዞ ቅሬታ ከቀረበባቸው በርካታ ክለቦች መካከል ጅማ አባ ጅፋር እግር ኳስ ክለብ ሌላኛው ሲሆን፤ክለቡ ለተጫዋቾቹ ደመወዝ ከከፈለ ሰባት ወርና ከዚያም በላይ እንደሆነው በተጫዋቾቹ በኩል ቅሬታዎች ሲቀርቡ እንደነበር ይታወሳል።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሪሚየር ሊጉን ጨምሮ በየደረጃው የሚወዳደሩ ክለቦች በኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ውድድር ቢያቋርጡም፣ ተጨዋቾቻቸውን በተመለከተ ግን በገቡት ውል መሠረት ክፍያ መፈጸም እንዳለባቸው የሚያስገድድ ደንብ አለው፡፡ክለቦች በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት የተቋረጠውን እግር ኳስ እንደገና ለማስጀመር በአንዳንድ ክለቦችና ተጫዋቾች መካከል ከወርኃዊ ክፍያ ጋር በተያያዘ የተፈጠረው ከፍተኛ ችግር እንቅፋት እንደሆነ ይወሳል፡፡ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በክለቦችና በተጫዋቾች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት፣ ክለቦች በገቡት የውል ስምምነት መሠረት የተጫዋቾቻቸውን ወርኃዊ ክፍያ እንዲከፍሉ ያስተላለፈው ተደጋጋሚ መመሪያና ማስጠንቀቂያ መፍትሔ ሊሆን እንዳልቻለ የሚናገሩ አሉ፡፡እንደ ሰበታ እግር ኳስ ክለብም ሆነ ሌሎች ክለቦች ይህንን መመሪያ ተፈጻሚ ለማድረግ ፍላጎት እያሳዩ አለመሆናቸው እየተነገረ ይገኛል ።በተለያዩ ክለቦች በኩል እየቀረቡ ያሉት ቅሬታዎች ጊዜ የማይሰጡ እንደመሆናቸው ብሄራዊ ፌዴሬሽኑም ሆነ ክለቦች በመነጋገር መፍትሄ መስጠት እንደሚኖርባቸው በሙያተኞች በኩል ሀሳብ እየቀረበ ይገኛል።የኮቪድ -19 ወረርሽን ተከትሎ በፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ክለቦች አካባቢ እየታየ ያለው የፋይናንስ መቃወስ ከተጫዋቾች ቅሬታ ተሻግሮ የሀገራችን እግር ኳሱ ህልውና አደጋ ላይ የመውደቁ ተጨባጭ ምልክት ነውና መፍትሄ ማበጀት ይገባል ባይነን።አዲስ ዘመን ሐምሌ10/2012 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "296b20856d18f756824308f17708ecdb" }, { "passage": "የዓለም አትሌቲክስ በየጊዜው የሚያስተላልፋቸው አዳዲስ ውሳኔዎች የስፖርቱን ቤተሰብ በማስከፋት የቀጠለ ይመስላል።የዓለም አትሌቲክስ በራሱ በሚያጸድቃቸው ሃሳቦች በበርካቶች ዘንድ ተቃውሞም ይቀርብበታል፤ ይሁን እንጂ ተግባራዊ ከማድረግ ወደ ኋላ አላለም።ከእነዚህ መካከል አንዱ በዳይመንድ ሊግ ይካሄዱ የነበሩ ውድድሮች መቀነሳቸው ነው።ሃሳቡ በተነሳበት ወቅት ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካዊያን የስፖርት ማህበራት ተቃውሟቸውን ቢያሰሙም ተቀባይነት ሊያገኙ ሳይችሉ ወደ ውሳኔ ተቀይሯል።ከአዲሱ የፈረንጆች አመት ጀምሮም ከዳይመንድ ሊግ እንዲቀነሱ የተደረጉ ውድድሮችን ተከትሎ በርካቶች ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ።በተለይ የአሜሪካ አትሌቶች ለጥያቄ ያመቻቸው ዘንድ ማህበር በመመስረት ላይ የሚገኙ መሆኑን ሜይል ኦንላይን አስነብቧል።በርዝመት ዝላይ የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑ ክርስቲያን ቴይለር በጉዳዩ ላይ አትሌቶች መታገል እንዳለባቸው በማህበራዊ ገጾች በመጠቀም አትሌቶችን እያነሳሳ ይገኛል።አትሌቱ በመግለጫው ላይ ስፖርቱን እያጠፉት መሆኑን የጠቀሰ ሲሆን፤ ለአትሌቶች መብት መታገል እንደሚገባም ገልጧል።ስፖርቱ እንዲያድግም መሰል ድርጊቶች መቆም እንዳለባቸውም ነው ያመላከተው። የውድድሩ አዘጋጆች ውድድሮቹ በቴሌቪዥን ሲተላለፉ ሳቢ እና ማራኪ እንዲሆኑ በማሰብ የቀነሷቸው የውድድር አይነቶች ላይ የዓለም አትሌቲክስ አሸማጋይ የሆነ ሃሳብ ከማንሳት ይልቅ ድጋፉን መስጠቱ ያበሳጫቸው አትሌቶችም ደብዳቤ ለዓለም አቀፉ የበላይ አካል ጽፈዋል።‹‹ውድድሩ በዓለም ህዝብ ዘንድ ሳቢ እንዲሆን ለውጦች መዳረጋቸውንና ማስፈለጋቸውን ብናምንም የዓለም አትሌቲክስ ግን አትሌቶችን ከግንዛቤ ያስገባ አይመስልም።በውሳኔው ላይ አትሌቶች አስተያየት እንዲሰጡ አለመደረጉም  ትክክል አይደለም›› ሲሉም አክለዋል።ማህበሩን በርካታ አትሌቶች እየተቀላቀሉት ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል እንግሊዛዊያኑ የዓለም ቻምፒዮን ዲያና አሸር ስሚዝ እንዲሁም የቀድሞው ርዝመት ዝላይ አትሌት ጆናተን ኤድዋርድስ ይጠቀሳሉ።አንጋፋው አትሌት የዓለም አትሌቲክስ በርካታ ስህተቶችን በመስራት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።ሆኖም ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው አካል አስካሁንም የሰጠው ምላሽ ወይም አስተያየት የለም።አዲስ ዘመን ጥቅም4/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "652b4dd6b1e8c6139964a6410e79018c" }, { "passage": "የወቅቱ የዓለም ራስ ምታት በሆነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች አንቀላፍተው ቢቆዩም ከሰሞኑ የአውሮፓ ሊጎች ወደ ልምምድ መመለስን ተከትሎ የስፖርቱ ኢንዱስትሪ መነቃቃት ጀምሯል። አሁንም የኮሮና ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) ስጋት እንዳለ ቢሆንም ጥንቃቄን በተላበሰ መልኩ ወደ ቀድሞው መደበኛ ሁኔታ ለመመለስ ጥረቶች እየታዩ ነው። በዚሁ ምክንያት ተቀዛቅዞ የቆየው አበረታች ቅመሞችን መከላከልና የመቆጣጠር ሥራ ነው። ይህ ስፖርትን በተፈጥሯዊው መንገድ ብቻ እንዲካሄድ የማድረግ ጥረት ሊቀዛቀዝ የቻለው በዓለም አቀፍ ደረጃ ውድድሮች መቋረጣቸውን ተከትሎ ነው። ይሁን እንጂ ከዓላማው አንጻር ረጅም ጊዜ መውሰዱና መዘናጋቱ ዋጋ ሊያስከፍል ይችላል። \nበመሆኑም ዓለም አቀፉ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በስሩ ለሚገኙት ብሔራዊ ጽሕፈት ቤቶች መመሪያ ማዘጋጀቱን ከሰሞኑ በድረገጹ አስነብቧል። ይህም በየሀገራቱ የሚገኙ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ጽሕፈት ቤቶች ወደ ቀደመ ሥራቸው እንዲመለሱ የሚያስችል ርምጃ ነው። ኤጀንሲው በወረርሽኙ ምክንያት በዓለም ዙሪያ ሲሰሩ የቆዩት ናሙና የመውሰድና ምርመራ የማድረግ ሂደቶችን የቀነሰና አንዳንድ ሥራዎችንም በጊዜያዊነት ማቋረጡን በዘገባው ተጠቁሟል። ነገር ግን አሁን ወደ ሥራ ለመመለስ እንቅስቃሴ መደረግ እንዳለበት የኤጀንሲው ፕሬዚዳንት ዊቶልድ ባንካ ይገልጻሉ። በኤጀንሲው ስር ካሉ ተቋማት ጋር ከወቅታዊው ጉዳይ ጋር በተያያዘ በቅርበት ሲሰሩና ድጋፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል። አሁን ግን ሥራው እንደቀድሞው መቀጠል ያለበት በመሆኑ፤ በቴክኖሎጂ በታገዘና የናሙና አወሳሰዱን በአዲስ መንገድ ማካሄድ ተገቢ መሆኑን ያመላክታሉ። ለዚህ ደግሞ በጸረ አበረታች መድኃኒት ቁጥጥር ላይ የሚሰሩ አካላት አዲስ ነገር ለመፍጠር ርብርብ ላይ ይገኛሉ። \nየተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኦሊቨር ኒግሊ በበኩላቸው፣ በዚህ ወቅት ናሙናዎችን ከአትሌቶች ለመውሰድ አዳጋች መሆኑን ነው የሚጠቁሙት። ምርመራው መቀጠል የሚገባው አስፈላጊው የጤናና ንጽህና ሁኔታ የተስተካከለ ሲሆን ብቻ ነው። የአትሌቶችና በዙሪያቸው ያሉ አካላት ጤናም ኤጀንሲው ትኩረት የሚሰጠው ቀዳሚ ጉዳይ ነው። ተቋሙ የአትሌቶችን ናሙና በመውሰድ አበረታች መድኃኒት ተጠቃሚነታቸውን በምርመራ መለየት ብቻም ሳይሆን የጤና ግለ ታሪካቸውንም መመዝገብ ሌላው ተግባሩ ነው። ንጹህ ስፖርት ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ግንዛቤ ማስጨበጥም እንዲሁ። በመሆኑም በቀጣይ ሳምንታት ከብሔራዊ ተቋማቱ ጋር በመሆን ሥራው በምን መልኩ መቀጠል ይገባዋል በሚለው ላይ መፍትሄ በማፈላለግ ወደ ሥራ የሚመለስ እንደሆነ አብራርተዋል።\nየሯጮቹ ሀገር ኢትዮጵያም የኤጀንሲው አባል ሀገር በመሆን ንጹህ ስፖርት እንዲካሄድ ሚናቸውን ከሚወጡት መካከል ትጠቀሳለች። ተሞክሮውን ለሌላው ዓለምም ማጋራት የቻለና በሥራው ምስጉን የሆነ ጽሕፈት ቤትም በአጭር ጊዜ ለማቋቋም መቻሉ ይታወቃል። በመላው ዓለም ባጠላው በዚህ የወረርሽኝ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ጽሕፈት ቤት እንቅስቃሴውን በምን መልኩ እያከናወነ ይገኛል? የሚለውን የጽሕፈት ቤቱ ዳይሬክተር አቶ መኮንን ይደርሳል ያስረዳሉ። የተቋሙን ውስጣዊና ውጫዊ እንቅስቃሴ በሁለት የሚከፍሉት ዳይሬክተሩ፤ የኮሮናን ቫይረስ በመከላከል ረገድ ሠራተኞችን የመቀነስና የንጽህና ቁሳቁስን የማዘጋጀት ሥራዎች መከናወናቸውን ይጠቁማሉ። \nሁለተኛውና ከተቋሙ ውጪ ከአትሌቶች ጋር በመገናኘት የሚከናወነው ደግሞ ከአበረታች መድኃኒት ቁጥጥር ጋር የተያያዘው ሥራ ነው። ይሁን እንጂ ከአትሌቶች ናሙና መውሰድ በእጅጉ ለንክኪ የሚያጋልጥ በመሆኑ አትሌቶችንም ሆነ በምርመራው ተሳታፊ የሆኑ ባለሙያዎችን ለቫይረሱ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በማሰብ ለጊዜው ገታ ተደርጓል። \nነገር ግን ሥራውን ሙሉ ለሙሉ ማቆም የማይቻል በመሆኑ ለቫይረሱ አጋላጭ ይሆናሉ የሚል ስጋት ያሳደሩ ሥራዎችን ፎርማት ለመቀየር መሞከሩን ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። በዚህም መሠረት አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቃሚ የሆኑ አትሌቶችን የማጋለጥ፣ አትሌቶች ባዮሎጂካል ፓስፖርት ፕሮግራም ሥራን የማጠናከር እንዲሁም ሌሎች ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህ ጊዜ ውድድሮች የተቋረጡ ቢሆንም ስፖርተኞች ግን በየግላቸው በቤታቸው ውስጥ እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን አላቆሙም። ይህንን ተከትሎም ከውድድር ውጪ የሚወሰዱ አበረታች ንጥረ ነገሮችን ከመውሰድ እንዲቆጠቡም ያሳስባሉ። በጥቅሉ በጊዜያዊነት ንክኪ ካለባቸው ሥራዎች በቀር ሌሎች ሥራዎች እንደቀጠሉ ሲሆን፤ የአድራሻ ምዝገባቸውን በመደበኛ መልኩ የሚያደርጉ በመሆኑ በዚህ ላይም መዘናጋት አይገባም።\nዓለም አቀፉ የጸረ አበረታች መድኃኒቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በመግለጫው ባመላከተው መሠረት፤ ጽሕፈት ቤቱም እንደቀደመው የአትሌቶችን ናሙና ወደመውሰድና መመርመር ሥራው ለመመለስ የሚያስችለውን ሁኔታ እያጠና ይገኛል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከሆነም ስፖርተኞች ከባለሙያዎች ጋር የሚኖራቸውን ንክኪ በሚቀንስና ለበሽታው አጋላጭ በማይሆን መልኩ መፍትሄ እንደተገኘ በቀጥታ ምርመራው የሚጀመር ይሆናል። በብሔራዊ ቡድን፣ በክለብ እና በማሰልጠኛ ተቋማት የተያዙ አትሌቶች እንዲሁም በቡድን ሆነው የሚሰሩ ሰልጣኞች በዚህ ወቅት ልምምድ አቋርጠው በቤታቸው ይገኛሉ። ምንም ዓይነት የቡድን እንቅስቃሴ የማይፈቀድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አትሌቶች በያሉበት አነስተኛ ልምምድ ብቻ የሚያደርጉ ይሁን እንጂ አሁንም እንደ ተቋም አስጊ ሁኔታዎች መኖራቸው አልቀረም። \nይህም ወቅታዊውን ሁኔታ ሽፋን በማድረግ የተከለከሉ ንጥረነገሮችን የመጠቀም አዝማሚያ ሊኖር ይችላል የሚል ስጋት ነው። እስካሁን በተጨባጭ የተገኘ መረጃ ባይኖርም በዓለም አቀፍ ደረጃም ሆነ እንደ ተቋም ስጋቱ አለ። ከአትሌቶች ባሻገር ከጀርባ በመሆን አጋላጭ የሆኑ አካላት አበረታች ቅመሞችን እንዲጠቀሙ በመገፋፋትና በማሳመን የሕግ ጥሰት የመፈጸም አዝማሚያ ሊኖር ይችላል የሚል ግምት አለ። በመሆኑም ስጋቱን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ ነው የሚገኙት። \nበስፖርተኞች በኩል ስለ ጉዳዩ ያለውን ግንዛቤ ለማስፋትም በመገናኛ ብዙኃን በመታገዝ መልዕክቶች በመተላለፍ ላይ ይገኛሉ። በተመረጡ መገናኛ ብዙኃን ላይም የማስታወቂያ እንዲሁም የማንቂያ ሥራዎች እየተካሄዱ መሆኑን የሚጠቁሙት ዳይሬክተሩ በጽሕፈት ቤቱ ድረገጽም መረጃዎችን እያስተላለፉ ይገኛል። ይህም አትሌቱ በሚመቸው መንገድ መረጃ እንዲያገኝ ያስችለዋል። በቀጣይም በመደበኛነት ማስታወቂያዎቹ የሚተላለፉባቸውን የመገናኛ ብዙኃን ቁጥር ለመጨመር ታቅዷል። ሌላው ጽሕፈት ቤቱ በትኩረት እየሄደበት ያለው የሕግ ማዕቀፍ የማሻሻል ሥራ ነው። ኤጀንሲው የጸረ አበረታች ቅመሞች ሕግን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን አሻሽሏል፤ በመሆኑም በጽሕፈት ቤቱ በኩል እአአ በ2021 ተግባራዊ የሚሆኑ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን ለመከለስ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። \nበመጨረሻም ዳይሬክተሩ ስፖርተኞችም ሆኑ ሌሎች የሀገሪቷ ዜጎች የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በመተግበር በዓለም ላይ ከተከሰተው ወረርሽኝ ራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ስፖርተኞች፣ የስፖርት ባለሙያዎች፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው በአበረታች ንጥረ ነገር መከላከልና መቆጣጠር ሥራው ለአፍታ የቆመ ባለመሆኑ መዘናጋት እንዳይኖር ዳይሬክተሩ ያሳስባሉ። ዓለም አቀፉ ኤጀንሲም ሆነ የዓለም አትሌቲክስ ይህ ጊዜ ሲያልፍ ስፖርቱ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በጥንቃቄ እየተመለከቱት ነው። በዚህ መሠረት የሚመለከታቸው አካላት ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። ተጠቃሚነታቸው ከተረጋገጠም ጽሕፈት ቤቱ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እንዲሁም የወንጀል እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ የማይል በመሆኑ ስፖርተኛው በመደበኛ ጥንቃቄው መቀጠል እንዳለበት ዳይሬክተሩ አስቀምጠዋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 10/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "01f73fe2dd71eb57e86861f0d6e6addf" } ]
bcaef4b0e1ff4b26f46a8be220ecc18f
83694b27e4ed57c766428f100aef4977
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ የመንገድ፣ የወደብ አገልግሎቶችንና የመኪና ማቆሚያ ጣቢያዎችን ለማሻሻል ተስማሙ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ የመንገድ፣ የወደብ አገልግሎቶችንና የመኪና ማቆሚያ ጣቢያዎችን ለማሻሻል መስማማታቸው ተገለጸ:: በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ከጅቡቲ ወደቦች ዓለም አቀፍ ነፃ የንግድ ቀጠና ሊቀመንበር አቶ አቡባከር ኦመር ሀዲ ጋር የመንገድ፣ የወደብ አገልግሎቶችንና የመኪና ማቆሚያ ጣቢያዎችን ለማሻሻል ተስማምተዋል:: አምባሳደር ብርሃኑ፣ ለሁለቱ አገራት ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክተው የዲኪል-ዳጉሩ መንገድ በፍጥነት ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ክትትል እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል::የመንገዱ ግንባታ ቀሪው 80 ኪሎ ሜትር መንገድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመጀመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መክረዋል:: የዶራሌ ሁለገብ ወደብና የጅቡቲ ኮንቴይነር ተርሚናልን ከኢትዮጵያ-ጅቡቲ የባቡር ሀዲድ ጋር በማገናኘት የወደብ አገልግሎቶችን አቅም ማሻሻል በሚቻልባቸው ሁኔታ ላይ መምክራቸውንም ነው አምባሳደሩ የገለጹት:: ጅቡቲ በሆራይዘን ነዳጅ ማደያንና በአዋሽ የሚገኘው የኢትዮጵያ የነዳጅ ማከማቻን ከኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር ጋር ለማገናኘት ከስምምነት ተደርሷል። ይህም የነዳጅ ጭነት ፍሰት በማቀላጠፍ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለመከላከል ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሏል:: ከደረቅ የመኪና ማቆሚያ ተርሚናል ጋር ተመሳሳይ የሆነ አስተዳደራዊ አሠራር ለማስቀመጥ ለነዳጅ ተርሚናል የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ እንዲሰጥ የኢትዮጵያ መንግሥት ያቀረበው ጥያቄም በወደብ እና በነፃ ዞን ባለሥልጣን ተቀባይነት አግኝቷል:: ሊቀመንበሩ የባለቤትነት ማረጋገጫ ወረቀቱን ለኢትዮጵያ ወገን በፍጥነት ለመስጠት ቃል መግባታቸቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል::አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38387
[ { "passage": "የኢትዮጵያ የባህር ትራ ንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የሎጅስቲክስ አገልግሎትን ፈጣንና ዘመናዊ ለማድረግ የደረቅ ወደብ ማስፋፊያዎችን እየሠራ ነው። ለወደብ ማስፋፊያዎችም ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር በጀት መያዙን አመልክቷል። የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ሥራ\nአስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ እንደገለጹት፤ ሞጆ ላይ ለሚሰራው የደረቅ ወደብ ማስፋፊያ በዓለም ባንክ በጀት 150 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት ተይዟል። በቀጣይም እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ይሰራል። ይህም ሞጆን ትልቅ የሎጅስቲክስ ከተማ ለማድረግ የሚያስችል ይሆናል፡፡ ግንባታውን በዘመናዊ ማሽኖችና ቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን ልዩ\nትኩረት መሰጠቱን ሥራ አስፈፃሚው ተናግረው፣ በአሁኑ ወቅት ዘመናዊ የወደብ ማስተናገጃ ዕቃዎች መገዛታቸውንና ተጨማሪ መጋዘኖችም እየተገነቡ መሆኑን አስታውቀዋል። ድሬዳዋ ከተማ\nላይ ዘመናዊ ደረቅ ወደብ በ69 ሚሊዮን ዶላር\nእየተገነባ እንደሆነም አቶ ሮባ ገልፀው ፣ በተመሳሳይ ኮምቦልቻ ከተማ\nላይ በ25 ሄክታር መሬት ላይ ደረቅ ወደብ እየተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል። በደቡብ ጎንደር ወረታ እና መቐለ ላይም ደረቅ ወደብ ግንባታ እየተሠራ ሲሆን በሌሎች አካባቢዎችም የሚጀመር መሆኑን አስገንዝበዋል። ለደረቅ ወደብ ማስፋፊያዎች የትራንስፖርት ችግሩን ለመፍታት ከፍተኛ የመጫን አቅም ያላቸው 150 ከባድ ተሽከርካሪዎች ተገዝተዋል። የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎቱን ለማዘመን ከዓለም አቀፍ ወኪሎች ጋር በምክክር መድረክ የልምድ ልውውጥ እንደሚደረግ ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። የአገሪቱ የወጪ ንግድ ተወዳዳሪ እንዲሆን ከተለያዩ የዓለም አገራት ወኪሎች ጋር በጋራ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ‹‹የሎጅስቲክስ አገልግሎት አፈፃፀም ከሚለካባቸው ነገሮች አንዱ መሰረት ልማት ነው›› ያሉት አቶ ሮባ፤ የትራንስፖርት አገልግሎት ተግዳሮት እንዳይሆን በኮሪደሮች አካባቢ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት 3 ሚሊዮን 855 ሺ 248 ቶን ጭነቶች አጓጉዟል። 796 ሺ 955 በራሱ መርከቦች ሲሆን የተቀሩት 3 ሚሊዮን 58 ሺ 293 ቶን ጭነቶች በሌሎች አገራት መርከቦች የተጓጓዙ ናቸው። አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 8/2011ዋለልኝ አየለ", "passage_id": "f7bf590f65113f6c377efd5f15b32685" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ የሚገኘው የጅቡቲ ውሃ ፕሮጀክት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ የመጀመሪያ ምዕራፍ መጠናቀቁ ተገልጿል፡፡የውሃ ፕሮጀክቱ በሶማሌ ክልል አዲጋላና ኩለን ከተሞች መካከል የተገነባ ሲሆን÷ 28 ጉድጓዶች እና ሁለት የውሃ ማጠራቀሚ ፓምፕ ጣቢያዎች አሉት ተብሏል፡፡የተዘረጋው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ስምንት ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል የሚጠቀም መሆኑ ተገልጿል።የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማ የሁለቱን ሃገራት ህዝቦች የእርስ በእርስ ግንኙነት ለማጠናከር፣ የጅቡቲ ህዝቦችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ እና ከሃይል ሽያጭ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ወጪ 49 ሚሊየን ብር መሆኑን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡የተዘረጋው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ጥራቱን የጠበቀና የጅቡቲን ህዝቦች የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል ሲሆን÷ የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ምዕራፍ በቀጣይ የሚከናወን ይሆናልም ነው የተባለው፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ የድሬዳዋ አስተዳደር ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ የ12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ጥንድ 33 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር መዘርጋቱ ተገልጿል፡፡\nየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "33d270677399028f5227256c05a48b83" }, { "passage": "ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ ኢትዮ- ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያዊያንና ጅቡቲያዊያን ካፒቴኖች እንደሚያዝ የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ጥላሁን ሳርካ አስታወቁ። ጥላሁን ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፤ ትራንስፖርት ስራው በይፋ ከተጀመረ 19 ወራትን ቢያስቆጥርም ባቡሩን በማንቀሳቀስ ረገድ ኢትዮጵያዊያን ሚናቸው አናሳ እንደነበርና እንዲያውም ሙሉ በሙሉ በቻይናዊያን ካፒቴኖች እንደሚንቀሳቀስ ተናግረዋል።ይህንም ለመቅረፍ 65 ያህል ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያዊያን የባቡር ካፒቴኖችን ወደ ቻይና በመላክ ለማሰልጠን እንደታቀደ ኢንጅነር ጥላሁን ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ቻይናዊያን ፕሮፌሰሮችና ረጅም ልምድ ያላቸውን የባቡር ካፒቴኖች ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ስልጠና ይሰጥ የነበረ ቢሆን በቂ እንዳልሁነ መንግስት መገንዘቡንም ጥላሁን ገልፀዋል። አዲሱ እና በቻይና አገር የሚሰጣቸው ስልጠና ግን ሙሉ በሙሉ ስልጠናውን ቃጠናቀቁ በኋላ ለጥቂት ጊዜያትም እዛው ቻይና ውስጥ ባቡር እንደሚያሽከረክሩም ተገልጿል።በቻይናው የኮንስትራክሽን ኩባንያ ሲሲኢሲሲ እና ሲአርኢሲየተገነባው ኢትዮ- ጅቡቲ ምድር ባቡር በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ ጠንካራ ሥራ እየተሰራበት የሚገኝ ሲሆን ከካፒቴኖች በተጨማሪም በቀጣይ ደግሞ የጥገና ባለሙያዎችን እና ዋና መቆጣጠሪያ ጣቢያ የሚሰሩ ሰራተኞችንም ቀስ በቀስ በኢትዮጵያዊያን እንደሚተኩ አዲስ ማለዳ አረጋግጣለች።", "passage_id": "8d637c2a528ffe587187dd1a8b50b102" }, { "passage": " – የኢትዮጵያ መንግስት 300 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ የተደረገባቸውን ዘጠኝ መርከቦች ዛሬ በጂቡቲ ተረከበ።ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝ በርክክብ ስነስርአቱ ላይ ፥  መርከቦቹ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን  የጂቡቲም ንብረት ናቸው ብለዋል።የመርከቦቹ ግንባታ የኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ማሳያ ናቸውም ነው ያሉት ።በዘጠኙ የሀገራችን የክልል ዋና ከተሞች የተሰየሙት እነዚህ መርከቦች ፥ ከቻይና መንግስት በተገኘ ብድር ነው የተገነቡት።የጂቡቲው ፕሬዝዳንት ኦማር ጉሌህ በበኩላቸው ፤ ሁለቱ ሀገራት የቆየና የተጠናከረ የህዝብ ለህዝብና የንግድ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው፥ ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የወደብ አገልግሎት ጂቡቲ ለራሷ የምታደርገው ያህል እንደሚሰማት ተናግረዋል።ፕሬዝዳንት ኦማር አክለውም ፥ የሀገራቱ ሁለንተናዊ የጋራ ተጠቃሚነት ተጠናክሮ ይቀጥላል ፤ አዲሶቹ መርከቦችም ኢትዮጵያ ለተያያዘቸውን ፈጣን እድገት መሰላል ይሆናሉ ብለዋል።(ኤፍ.ቢ.ሲ.)", "passage_id": "e1cf4c4675c5538c3fff0be8b2c6dcec" }, { "passage": "የጅቡቲን ወደብ በጋራ በማልማት ኢትዮጵያ የንግድ ባለድርሻ በምትሆንበት ሁኔታ  የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ከስምምነት ላይ ደረሱ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በጅቡቲ የሁለት ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል።በዚሁ ጉብኝታቸው  የጅቡቲ ወደብን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የተመራው ልዑክ ከጂቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማዔል ኦማር ጊሌ እና ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክሯል።የሁለቱን አገሮች ለዘመናት የቆየ ማህበራዊ ግንኙነት ከማጠናከርና ኢኮኖሚያዊ ትስስራቸውን ከማጎልበት አኳያ የተለያዩ ስምምነቶችም ተደርገዋል።ከስምምነቶቹ መካከል የጅቡቲን ወደብ በጋራ ለማልማትና ኢትዮጵያ የንግድ ባለድርሻ እንድትሆን ለማድረግ የሚያስችለው ስምምነት ተጠቃሽ ነው።በተመሳሳይ የአገሮቹን ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ሲባል የጅቡቲ መንግስትም ከኢትዮጵያ ታላላቅ የመንግስት ተቋማት ላይ ድርሻ ወስዶ እንዲሰራም ጥሪ ቀርቦለታል።በዚህም በሁለቱ መሪዎች ደረጃ ስምምነት የተደረሰ ሲሆን፤ ለተግባራዊነቱ የሚሰራ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚቴም ተቋቁሟል።ሚኒስትሮቹም በቅርቡ በጥናት ላይ የተመሰረተ ወደ ተግባር የሚቀየር እቅድ እንደሚያወጡ ይጠበቃል።ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የሁለት ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመሩት ልዑካን ቡድን ያካሄደውን የስራ ጉብኝት አስመልክቶ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ \"ጉብኝቱ የተሳካና የአገሮቹን ትብብሮች የሚያጠናክሩ ስምምነቶች የተደረሰበት ነው\" ሲሉ ገልጸውታል።ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፤ ለዚህም ትልቁ ማሳያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ \"በወደቡ ላይ ድርሻ ይኑረን\" ብለው ያቀረቡት ጥያቄ ምላሽ አግኝቶ ከስምምነት መደረሱ ነው። (ኢዜአ)", "passage_id": "5486bbc44698c3a1ad4fb5129843dae9" } ]
d70c01d60b327c5350a7d87432d95b03
9bfe3902fcc7d47e7cbeccee5bd84b89
በመቀሌ ከተማ የባንክ አገልግሎት መስጠት ተጀመረ
አማንሚካኤል መስፍን መቐለ፡- በህግ ማስከበር ዘመቻው ምክንያት በመቐለ ከተማ ተቋርጦ የነበረው የባንክ አገልግሎት መጀመሩን የከተማዋ ከንቲባ አስታወቁ። ከንቲባው አቶ አታክልቲ ሃይለስላሴ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዛሬ እንዳስታወቁት፤ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከከተማዋ ነዋሪዎች ጋር ከሰሞኑ ባካሄደው ተከታታይ ውይይት የተነሳውን የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ በተደረገው የተቀናጀ ስራ ትናንት ከሰአት በኋላ ጀምሮ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። በጁንታው አማካኝነት በመቀሌ ከተማ ሆን ተብለው በተለቀቁ የህግ ታራሚዎችና ሌሎች ዘራፊዎች የተነሳ በከተማዋ ላይ የጸጥታ ችግር መኖሩን በማንሳት ጊዜያዊ አስተዳደሩ እንዲያስተካክልላቸው የከተማዋ ነዋሪዎች የጠየቁ ሲሆን፤ በትናንትናው እለት በነበረው የወጣቶች ውይይትም ወጣቱ የከተማውን ሰላምና ጸጥታ ከአስተዳደሩ ጋር ሆኖ ለመጠበቅ ቃል መግባቱ ይታወሳል።የከተማዋ ነዋሪና ጊዜያዊ አስተዳደሩ ባደረጉት የተቀናጀ ጥረትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎት ከዛሬ ከሰአት ጀምሮ ለህዝብ ክፍት ሆኖ ደንበኞች መጠቀም መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢ በየቅርንጫፎቹ ተገኝቶ ተመልክቷል። የግል ባንኮችም አገልግሎት መስጠት እንዲጀምሩ ትዛዝ እንደተላለፈላቸው የከተማዋ ከንቲባ አቶ አታክልቲ አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38393
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጂቡቲ የከፈተውን ቅርንጫፍ በትናንትናው እለት መርቀው ከፍተዋል።በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህን ጨምሮ በጂቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር አብዱላዚዝ መሃመድ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ባጫ ጊና እንዲሁም ሌሎች የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ በምረቃው ላይ፥ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጂቡቲ ቅርንጫፍ መከፈት የሀገራቱን ሁለንተናዊ ግንኙነት እንደሚያጠናክር ገልፀዋል።እንዲሁም የሃገራቱን ህዝቦች የንግድ ግንኙነት የሚያጠናክር እና የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑንም አስታውቀዋል።በተጨማሪም በጂቡቲ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እና በንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያንን የተሟላ የባንክ አገልገሎት እንዲያገኙ ያስችላልም ነው ያሉት።ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በወጪና ገቢ ንግድ፣ መሰረተ ልማት፣ በውሃ እና በኤሌክትሪሲቲ ስትራቴጂካዊ እና ሁለንተናዊ ግንኙነት አላቸውም ብለዋል።የቅርንጫፉ መከፈት በኢትዮጵያ እና በጂቡቲ ሪፐብሊክ መካከል የሚካሄደውን የኢኮኖሚ ውህደት ለማፋጠን የሚረዳ መሆኑንም ነው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ የገለፁት።", "passage_id": "d06a097cad6afe7d492ae17793cf0707" }, { "passage": "ከግብይትዎ በኋላ \"እስኪ ስልክህን/ሽን ንገረኝ/ንገሪኝ\" ብለው በተንቀሳቃሽ ስልክዎ አማካኝነት ክፍያ ሊፈጸሙ ይችላሉ።\n\n በአጭሩ ስልከዎ አንድ የባንክ መስኮት የሚሰጠውን አገልገሎት ማቅረብ ይችላል። እንዴት? \n\nይህ በእጅ ስልክ ገንዘብ የማንቀሳቀስ አስራር በበርካታ አገራት የተለመደ ሆኗል። \n\nጎረቤት ኬንያ ከ14 ዓመታት በፊት የጀመረችው 'ኤምፔሳ' የተሰኘውን የሞባይል ገንዘብ ስርዓት አሁን ላይ 72 በመቶ የሚሆነው የአገሪቱ ነዋሪ እየተጠቀመው ይገኛል ይላል ቮክስ ከተባል ድህረ ገጽ የተገኘ መረጃ። \n\nበሰባት አገራት የሚሰራው ኤምፔሳ 42 ሚሊዮን ንቁ ደንበኞችና 400 ሺህ ወኪሎች አሉት። \n\n50 በመቶ የሚሆነው የኬንያ ዓመታዊ ጥቅል ምርት [GDP] በዚሁ ስርዓት በኩል ይንቀሳቀሳል። \n\nበኡጋንዳ ከጠቅላላ ህዝቡ የባንክ አካውንት ያለው 11 በመቶ ሲሆን ኤምፔሳን የሚጠቀመው ሰው ግን 42 በመቶ ተሸጋግሯል። እናም እነዚህ አገራት ከግብይት በኋላ ቁጥርህ/ሽን ንገረኝ ማለት የተለመደ ነው። \n\nከትናንት በስትያ [ማክሰኞ ግንቦት 3 - 2013] ይፋ የሆነው ቴሌብር መሰል አገልግሎትን በኢትዮጵያ የማቅረብ አላማ ይዟል።\n\nየኢትዮጵያ ሞባይል ገንዘብ አገልግሎት - ቴሌብር\n\nከቢቢሲ ጋር ቆይታ የነበራቸው የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ኩባንያቸው ያሉትን መሰረተ ልማቶች ለድምጽ፣ ለጽሁፍ መልዕክትና ለኢንተርኔት አገልግሎት ብቻ ሲያውለው መቆየቱን አውስተዋል። \n\nታድያ ቴሌብር የተሰኘው አዲሱ አገልግሎት መሰረተ ልማቱን ገንዘብ ለመቀበል፣ ለመላክ፣ የግብይትና የአገልግሎት ክፍያን ለመፈጸምም እንዲውልና \"ክፍያን ለማሳልጥ\" እንዲያግዝም ያስችላል ሲሉ ያስረዳሉ። \n\nበተጨማሪም የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ከውጪ ሀገራት ገንዘብ መቀበል ይችላሉ ብለዋል ዋና ስራ አስፈጻሚዋ።\n\nበኢትዮጵያ የፋይናንስ አገልግሎቶች በባንክና መሰል ተቋማት ብቻ እየተሰጠ የቆየ መሆኑን የሚገልጹት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ ቴሌኮም ደግሞ ከቴሌኮም አገልግሎት በተጨማሪ የፋይናንስ ስርዓት ላይ መሳተፍ የሚችልበት የህግ ማዕቀፍ አልነበረም ብለዋል። \n\n\"አገልግሎቱን ለመስጠት የሚያስችል የቴክኖሎጂ ስርአቱን ቢዘረጋም ከባድ ያደረገው ግን ኢትዮቴለኮም ይህንን አገልግሎት መስጠት እንዲችል የሚያደርገው የህግ ማዕቀፍ ለማሻሻል የሄድንበት ርቀት ግን ረጅምም አስቸጋሪም እንዲሁም ፈተናም የነበረበትም ነው ሲሉ\" ተናግረዋል። \n\nሁለት ዓመት ከፈጀ \"ውጣ ውረድ\" በኋላ ግን ይህንን አገልግሎት መስጠት እንዲችል ኩባንያው የተቋቋመበት ደንብ ማሻሻያ ከተደረገበትና ከብሄራዊ ባንክ ፍቃድ ካገኘ በኋላ አገልግሎቱ በ10 ቀናት ውስጥ ይፋ መሆኑን ገልጸዋል። \n\nመሰል ስርዓቶችን ለመዘርጋት ከ ሁለት እስከ ሶስት ዓመታት ሊፈጅ እንደሚችል ያነሱት ፍሬህይወት 'ሆኖም ፍቃድ እንደምናገኝ ተስፍ በማደረግ በአምስት ወራት ዝግጁ አድርገናል' ብለዋል።\n\nከባንኮች ወደ ቴሌብር የገንዘብ ዝውውር ለመፍጠር ለሁሉም ባንኮች ግብዣ ልከናል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ባንኮቹን ለማስተናገድ የሚያስችል ስርዓት መዘርጋቱን ተናግረዋል። ንግድ ባንክ በሁለት ሳምንት ውስጥ 'ሲስተሙን ከኛ ጋር እንደሚያቀናጅ አሳውቆናል'ም ብለዋል። \n\nይህ ማለት ቀድሞ ያሉ የሞባይል ባንክ ስርዓቶች የአንድ ባንክ ደንበኛ መሆንን ይጠይቃሉ። በአንፃሩ ቴሌብር የየትኛውም ባንክ ደንበኛ መሆን ሳይሆን ሲምካርድን ብቻ ይጠይቃል።\n\nአገልግሎቱን እንዴት ማግኘት ይቻላል?\n\nኢትዮ ቴሌኮም አሁን ላይ 53 ሚሊዮን ደንበኞች ያሉት ሲሆን ከዚህ ውስጥ ደግሞ 25 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚ ናቸው። \n\n23 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ ስማርት ስልክ አላቸው። \n\nእናም እንደዋና ስራ አስፈጻሚዋ ገለጻ 23 ሚሊዮኑ... ", "passage_id": "fad021dd16d7c4aafddc53e15d502d4f" }, { "passage": "በትግራይ ክልል ከትናንት ሌሊት ጀምሮ የኢንተርኔትና የስልክ አገልግሎት መቋረጡ ተገልጿል። በኢንተርኔት ነፃነት ላይ የሚሰራው ኔት ብሎክስ የተሰኘው ድርጅትም ከዛሬ ዕለት ጥዋት ጀምሮ ኢንተርኔትና የስልክ አገልግሎት መቋረጡንም አስታውቋል።ከዚህም በተጨማሪ ከጥዋት ጀምሮ የመብራት አገልግሎት ተቋርጧል፤ ባንኮች ተዘግተዋል።መቀሌ የሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ እንደገለፀው ኢትዮ-ቴሌኮም መስሪያ ቤት የተዘጋ ሲሆን ሰራተኞችም በሩ አካባቢው ይታያሉ ብሏል።በርካቶች በእግር እየተንቀሳቀሱ ሲሆን በህዝቡም ዘንድ ግራ የመጋባት ሁኔታ እንደሚታይና ዝርዝር መረጃዎች እየወጡ እንዳልሆነ በተጨማሪ ገልጿል።በአሁኑ ሰዓት የትግራይ ክልል ቴሌቪዥንም ሆነ ድምፂ ወያነ የሚሰሩ ሲሆን የተለመደ ፕሮግራማቸውን እያስተላለፉም ይገኛሉ።ከትናንት አመሻሽ ጀምሮ በትግራይ ክልል ውስጥ በአንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ኃይሎች ሲንቀሳቀሱ እየታየ የነበረ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዛሬው እለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ክልሉን በሚያስተዳድረው ሕወሃት ላይ ጦርነት መከፈቱን አስታውቀዋል።ጠቅላይ ሚንስትሩ በአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው የመከላከያ ሠራዊት በኮማንድ ፖስት እየተመራ \"ሀገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትእዛዝ ተሰጥቶታል\" ብለዋል።ትናንት ሌሊት (ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም) ወደ አምስት ሰዓት አካባቢ በመቀሌና አስራ አንድ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ኩዊሃ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ ይሰማ እንደነበር የቢቢሲ ዘጋቢ ከስፍራው አድርሷል።እስካሁን ድረስ ከትግራይ ክልል በኩል ምንም አይነት መረጃ ያልተገኘ ሲሆን የህወሃት ከፍተኛ አመራር ጌታቸው ረዳ ትናንት ሌሊት \"ወንድምና እህቶች ተረጋጉ\" በማለት በፌስቡክ ገፃቸው አስፍረው ነበር። ", "passage_id": "5819c02b629a4a40549178a6db2a9e75" }, { "passage": ". ወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ሊጀምር ነውአዳማ፡- የፌዴራል ህብረት ሥራ ኤጀንሲ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን የፋይናንስ አገልግሎት ሁሉን አቀፍና ደንበኛ ተኮር ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገለፀ፡፡ ወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ሰነድ አዘጋጅቶ ከእስልምና ሃይማኖት መሪዎች ጋርም መክሯል፡፡የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡስማን ሱሩር ትናንት በአዳማ በተካሄደው የምክክር መድረክ ላይ እንደተናገሩት፤ ኤጀንሲው በፋይናንስ ዘርፉ የሚሰጠውን አገልግሎት ደንበኛ ተኮር ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡ ለዚህ ተግባሩ ውጤታማነት ይረዳው ዘንድም በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ስራ ማህበራት አማካይነት የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎትን በሀገር ደረጃ ለማስጀመር በዘርፉ ልምድና ተሞክሮ ካላቸው አካላት ጋር በመሆን የትግበራ ሰነድ አዘጋጅቷል፡፡እንደ አቶ ኡስማን ገለጸ፤ የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት በተለያዩ አገራት በተለይም በሙስሊም አገራት ረጅም ዕድሜ ያስቆጠረ ሲሆን፤ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ከሃይማኖት አስተምህሮቶች ጋር በተጣጣመ ሁኔታ በተለያዩ የእስያ፣ አውሮፓ እና አፍሪካ አገራት በመስፋፋት ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ደግሞ አገራት ዜጎቻቸው በአገራዊ ልማት ውስጥ ፍትሃዊ ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን እንዲያረ ጋግጡ በማድረግ አገራዊ ሰላምና መረጋጋትን ለመገንባት እንዲችሉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው፡፡በኢትዮጵያ አገልግሎቱን የሚፈልግ የኅብረተ ሰብ ክፍል ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ የፋይናንስ አገልግሎቱን ደንበኛ-ተኮር በማድረግ ለህብረተሰቡ ማቅረብ በመሆኑ፤ አንዳንድ የፋይናንስ ተቋማት የአሰራር ማዕቀፍ በማዘጋጀት አገልግሎቱን መስጠት ቢጀምሩም ዝርዝር ደንብና መመሪያ፣ የአሠራር ማኑዋል፣ አደረጃጀት፣ ተመጣጣኝ ዕውቀትና ክህሎት በዘርፉ ባለመኖሩ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ የህብረተሰብ ክፍሎች በሚጠበቀው ደረጃና ጥራት ተደራሽ ማድረግ ሳይቻል ቆይቷል፡፡የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት በዋናነት የእስልምና ሃይማኖት አስተምሮትን መነሻ ያደረገና የሸሪዓ ድንጋጌዎችን ተከትሎ የሚሰራ የፋይናንስ አገልግሎት መሆኑን የገለጹት አቶ ኡስማን፤ ተግባሩም ሃይማኖታዊና ሰብዓዊ ዕሴቶችን በመገንባት የጋራ መረዳዳትንና መተሳሰብን በሰዎች መካከል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኤጀንሲው ወደዚህ ተግባር መግባቱ አገልግሎቱን ከቀበሌ እስከ ፌዴራል ባለው አደረጃጀቶች እንዲስፋፋና እንዲያድግ በማድረግ ህብረተሰቡ አገልግሎቱን በቅርበት ማግኘት እንደሚያስችለው፤ በቂ ፋይናንስ አገልግሎት አቅርቦት ተጠቃሚ ያልሆነውን የህብረተሰብ ክፍል በተለይም ለአርሶና አርብቶ አደሩ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው አብራርተዋል፡፡በኤጀንሲው የፋይናንስ ሕብረት ሥራ ልማት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ዱፌራ በበኩላቸው፤ አገልግሎቱ በባንኮችና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት እየተሰጠ ቢሆንም፤ በተለይ ባንኮች አገልግሎቱን የሚሰጡት በአመዛኙ ለባለሃብትና ነጋዴው ነው፡፡ ማይክሮ ፋይናንሶችም ቢሆኑ የሙስሊሙን ማህበረሰብ በተለየ መልኩ እያገለገሉ አይደለም፡፡ በመሆኑም ኤጀንሲው ይሄን አገልግሎት ተግባራዊ ሲያደርግ ከቀበሌ እስከ ፌዴራል ያለውን ህዝብ ተጠቃሚ በማድረግ ቀደም ሲል አገልግሎቱን የማያገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑና የሙስሊሙ ማህበረሰብ በስፋት የሚገኝባቸው አካባቢዎች ላይ የነበረውን የፋይናንስ አገልግሎት ችግር ለማቃለል መሆኑን አስረድተዋል፡፡አዲስ ዘመን ጥር 10/2011በወንድወሰን ሽመልስ", "passage_id": "2a291f0d5c968adcd9e2dede63fdce39" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ክልል በሁሉም ወረዳዎች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በቅርቡ እንደሚከፍት የፓርቲው የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙት ኃላፊ ገለጹ፡፡ የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አወሉ አብዲ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ብልጽግና አገር አቀፍ ፓርቲ በመሆኑ ከትግራይ ክልል ጋር በሚኖረው ሕገ መንግሥታዊ ግንኙነት መሠረት አደረጃጀቱን በማስፋት በቅርቡ በክልሉ በሁሉም ዞኖች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ጽሕፈት ቤቶችን ይከፍታል፡፡ ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ክልል ነባራዊ ሁኔታ እስካሁን ትርጉም ባለው መልኩ እንቅስቃሴ እንዳልተደረገ የገለጹት አቶ አወሉ፤ ነገር ግን አሁን በአዲስ መልክ የትግራይ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ተቋቁሞ ሥራውን እየሰራ ስለሆነ በቅርብ ጊዜ በክልል፣ በዞኖች፣ በወረዳና በቀበሌ ደረጃ እንቅስቃሴ ይደረጋል ብለዋል። ፓርቲው በትግራይ ክልል\nብዙ ደጋፊዎች እንዳሉት\nየገለጹት አቶ አወሉ፤\nበህወሓት ውስጥ ያሉት\nከግማሽ በላይ አመራሮች\nየብልጽግና ፓርቲ ደጋፊ\nመሆናቸውን ጠቁመው፤ የሚከፈቱ\nጽሕፈት ቤቶች ላይ\nየአመራር እጥረት እንደማይገጥም\nተናግረዋል።የፓርቲው ሥራም ማሰልጠንና\nማደራጀት እንደሆነና የአመራር\nክፍተት እንዳይኖር የማብቃት\nሥራዎች እንደሚሰሩ ጠቅሰዋል። እንደ አቶ አወሉ ገለጻ፤ ብልጽግና የሕዝብ ብሶትና ችግር የወለደው የለውጥ ፓርቲ ነው። የአቃፊነትና የአካታችነት ፓርቲ ነው።ሕዝቡን እየከፋፈለ የሚሄድ ሳይሆን ሁሉም ያስፈልገኛል ብሎ የሚያምን ፓርቲ ነው።ከፓርቲው በተቃራኒ የቆሙት ጥቂት ኃይሎች ናቸው።እነዚህ ጥቂት ተቃራኒ ኃይሎች ሕዝቡን በየቤቱ በመሳሪያ የሚያስፈራሩት ቢሆንም ሕዝቡ አይቀበላቸውም።ምክንያቱም በትግራይ ክልል ያለው ሕዝብም የፓርቲውና የለውጡ ደጋፊ ነው። «ፓርቲው በፊት የነበሩ ግንባር ድርጅቶችና አጋር ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ ራሳቸውን አክስመው ተቀላቅለዋል።ነገር ግን ህወሓት ከውህደቱ ራሴን አግልያለሁ ብሎ ክልላዊ ፓርቲ ሆኖ ቀጥሏል።ህወሓት ራሱን ማግለሉ መብቱ ነው።ይሄ በጣም ልንኮራበት የሚገባ ነው።ያመኑበትንና የራሳቸውን አቋም የገለጹበት ሁኔታ ስለሆነ እንደ ችግር የሚታይ አይደለም።ነገር ግን ብልጽግና ባለው አገራዊና ክልላዊ አደረጃጀት የትግራይ ክልል ብልጽግና ፓርቲ እንዲቋቋም ተደርጓል። ጽሕፈት ቤቱ አዲስ አበባ ላይ ተከፍቷል በቅርቡም በትግራይ ክልል በሁሉም ወረዳዎች እንከፍታለን ብለን አቅደናል።ይህ አገራዊ ፓርቲ በሁሉም ክልሎች ላይ ተንቀሳቅሶ የራሱን ዓላማ ለሕዝቡ የሚሸጥበት ሁኔታ ይኖራል» ሲሉም አቶ አወሉ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ደረጃ የተቋቋሙ አንድ ላይ ተቀናጅተው ግንባር የፈጠሩበትና ኢህአዴግ በሚል ስሙ ለ27ዓመታት አገር ሲያተራምስ እንደነበር አውስተው አሁን ግን እነዚያን ችግሮች በማስተካከል እውነተኛ ፌዴራሊዝምን በተግባር በማሳየት የሕዝብ የማንነት (በተለይ የቋንቋ፣ የባህል፣ ራስን የማስተዳደር) መብቶችና ጥያቄዎች በአግባቡ መልስ እንዲያገኙ ብልጽግና ፓርቲ እየሰራ መሆኑን፤ በተለይም የኢህአዴግ ዋና ዋና ተግዳሮቶች የሚባሉትን ሙሉ በሙሉ አርሞ ወደ ፊት ለመጓዝ የተደራጀ መሆኑን አቶ አወሉ አስታውቀዋል። አዲስ ዘመን\nየካቲት 20/2012አዲሱ ገረመው", "passage_id": "42a5bd7df77e342779d1bc4136bff8df" } ]
eb792439de81f67850ee25cf10b5c499
c560eec5db24c93dbf1b1f3c26bfc0dc
የፌዴራል የዴሞክራሲ ተቋማት የጋራ ፎረም መተዳደሪያ ድንጋጌ ጸደቀ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የፌዴራል የዴሞክራሲ ተቋማት የጋራ ፎረም መተዳደሪያ ድንጋጌ ጅግጅጋ በተካሄደው የተቋማቱ የጋራ የምክክር መድረክ ቀርቦ ጸድቋል:: የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ጫላ ለሚ የፌዴራል ተጠሪ ተቋማት የጋራ ፎረም መተዳደሪያ ድንጋጌንም ለጉባኤ አቅርበው አጽድቀዋል::በመተዳደሪያ ድንጋጌው ዝግጅት ላይ ባለድርሻ አካላትና የህግ ባለሙያዎች መሳተፋቸውንና ሰፊ ውይይቶች መደረጉን አብራርተዋል:: መተዳደሪያ ድንጋጌውን ያቀረቡት አቶ ደበበ ወ/ጊዮርጊስ ሰነዱ ከመዘጋጀቱ በፊት በ9 ነፃና ገለልተኛ ሆነው በሚሰሩና ተጠሪ ተቋማት ከም/ቤቱ ጋር ያላቸውን ግንኙነት፣ ተጠያቂነት፣ ለህዝብ ያላቸውን ተደራሽነት፣ የበጀትና የሰው ሀብት አስተዳደራቸው እና ያጋጠማቸውን ችግሮች በተመለከተ የዳሰሳ ጥናት መደረጉን ገልጸዋል:: አክለውም የተዘጋጀው መተዳደሪያ ድንጋጌም የፎረሙ አባላት በመደበኛነት በመገናኘት የጋራ ዕቅድ የሚያወጡበትና የአፈጻጸም ግምገማ እና የምክክርና የልምድ ልውውጥ የሚፈጥሩበትን ምህዳር ይፈጥራልም ብለዋል:: በቀረበው ሰነድ ላይም ከተሳታፊዎች በርከት ያሉ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል::ተቋማቱ ‹‹የዴሞክራሲ ተቋማት›› ከሚባሉ ‹‹ነፃ ወይም ገለልተኛ ተቋማት ቢባሉ›› የሚል ሃሳብ ተነስቷል:: የም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ተቋማቱ ነጻና ገለልተኛ ሆነው የሚሰሩ ቢሆንም ተጠሪነታቸው ለም/ቤቱ በመሆኑ ‹‹ተጠሪ ተቋማት›› በሚል ቢጠሩ አግባብነት እንዳለው ጠቁመዋል:: የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ እና ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ሪፎርም ቀርቦ ምክክር ተደርጎበታል::የኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድን ሪፎርም ያቀረቡት ም/ኮሚሽነር አቶ ውብሸት አየለ ሲሆኑ ቦርዱ አንድ አዋጅ እና 29 ማስፈጸሚያ መመሪያዎችን ማውጣት፣ የሰው ሃይልን ማደራጀት፣ የምርጫ ቁሳቁሶችን ማሟላት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ እና የህዝብ ግንኙነት ተግባራት በዋናነት ማከናወኑን አብራርተዋል:: በተመሳይም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ሪፎርም በዋና ኮሚሽነር በዶ/ር ዳንኤል በቀለ ቀርቧል::ኮሚሽኑ ነጻና ገለልተኛ ሆኖ ለመስራት የሚያስችለውን የህግ ማዕቀፍ ከማሻሻል ጀምሮ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ከህዝብ ተወካዮች የተገኘው መረጃ ያመላክታል::አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38390
[ { "passage": "ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/2012 ዓ/ም (አብመድ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2ዐ12 ጥራትን፣ ተናባቢነትንና ተፈፃሚነትን በማረጋገጥ ሀገራዊ ለዉጡን ሊደግፉ የሚችሉ የሕግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን አንደሚሠራ አፈ-ጉባኤ ታገሠ ጫፎ አስታወቁ፡፡ለፓርላማ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት አሠራራቸውንና አደረጀጀታቸውን ፈትሾ በማስተካከል የኅብረተሰቡን የመልካም አስተዳደርና የልማት ችግሮችን በመፍታት የተጀመረውን ለውጥ ማስቀጠል እንደሚገባም አፈ-ጉባኤ ታገሠ ጫፎ ተናግረዋል፡፡ምክር ቤቱ በዘንድሮው ዓመት በ2ዐ11 ለምክር ቤቱ በዋና ኦዴተር ከቀረበው ሪፖርት ግኝት በመነሳት የተጓደሉ የአሠራር ሥርዓቶችን ፈትሾ በማስተካከልና የሀብት አስተዳደር ሥርዓትን በመዘርጋት የሀገሪቱ ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሠራ አፈ ጉባኤ ተናግረዋል፡፡በምክር ቤቱ በአምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ የሀገራዊ ምርጫ እና የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን፣ በምክር ቤቱ የጸደቁ አዋጆችን ከባለድርሻ አካላት ጋር ተፈፃሚነታቸውን በመከታተል ግልፅና ተዓማኒነት እንዲኖረው በማድረግ ረገድ ትልቅ ሥራ እንደሚጠብቅም አስረድተዋል፡፡ምክር ቤቱ በ4ኛ ዓመት የምርጫ ዘመኑ የምክር ቤት አባላት ከወትሮው በተለየ መልኩ በሚወጡ ሕጎች ዙሪያ ሰፊ ውይይትና ክርክር አንዲሁም ባለተለመደ መልኩ በተቃውሞና በድምፀ ተዓቅቦ፣ በአብላጫ ድምጽ ሕጐች መጽደቃቸውን አፈ ጉባኤው አስታውሰው ይህም በምክር ቤቱ ዴሞክራሲ እየጎለበተ መምጣቱን አመላካች በመሆኑ ዘንድሮም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ምክር ቤቱ በዋናነት ሕግ የማውጣት ተግባርን የሚያከናውን ሲሆን በ2ዐ11 ዓ.ም የወጡ ሕጎች በሀገሪቱ ከተጀመረው ለውጥ ጋር የሚጣጣምና አጋዥ የሆኑ ሕጐች ጸድቀው ወደ ተግባር መገባቱንም ገልፀዋል፡፡ምክር ቤቱ በ2ዐ11 ዓ.ም ባደረገው የክትትልና የቁጥጥር ሥራ አንዳንድ ተቋማት ላይ የሚስተዋሉ የአሰራር ክፍተቶችን በመለየት ችግሩን በዘላቂነት ለመፈታት የሚያስችሉ የአሠራር ሥርዓቶች የመዘርጋትና የመቋቋሚያ አዋጆችንም ጭምር እንዲሻሻሉ የማድረግ ሠራ መሠራቱን አፈ ጉባኤው አስታውሰዋል፡፡", "passage_id": "e03f426c21f8a00753dc2adbecfb530a" }, { "passage": " በሃገሪቱ የእምነት አኩልነትና ተቻችሎ የመኖር የሃይማኖት እሴትን ሊያጎለብት የሚችል ረቂቅ አዋጅ ማዘጋጀቱን የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስትሩ ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም እንዳሉት በሃይማኖቶች ስም የሚደረጉ የፖለቲካና ሌሎች እንቅስቃሴዎችን ለመግታት አንዲቻል የሃይማኖት መሪዎችና አባቶች የሚተገብሩት ረቂቅ ህግ ማውጣት አስፈላጊ ሆኗል ፤ በመሆኑም ረቂቅ አዋጁ ይህንን አሰራር እንደሚያሰፍን ታምኖበታል። መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ እንደማይገባ በህገ መንግስቱ መካተቱን ያስታወሱት ሚኒስትሩ ፥ ይህም በረቂቅ አዋጁ መደገፉን ነው ያብራሩት። እንደ ፋና ዘገባ የሃይማኖት ተቋማትና መንግስት በሰላምና በልማት እሴቶች ላይ በጋራ ተባብረው እንዲሰሩም ረቂቅ አዋጁ ድጋፍ ያደርጋል ተብሏል። ", "passage_id": "9d7f2f81be7cc05dedde59fec725c172" }, { "passage": "የአገሪቱ ሕዝቦች መስዋትነት በመክፈል ያጸደቁት  ሕገ መንግሥት በአገሪቱ የፌደራላዊ ሥርዓት ግንባታ አስተማማኝ  መሠረት እንዲኖረው  ዋስትና  የሠጠ መሆኑን   የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ያለው አባተ ገለጹ ።በጋምቤላ ክልል ከተማ እየተካሄደ ባለው ከ10ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና  ሕዝቦች  በዓል ጋር  በተያያዘ  በጋምቤላ ክልላዊ  መንግሥት ምክር ቤት በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ያለው አባት እንደገለጹት አገሪቱ ለተከታታይ 10 ዓመታት ያስመዘገበችው  ባለሁለት አሃዝ ዕድገት የሕገ መንግሥቱ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል ።10ኛው የብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል የሚከበረው የመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድን በማጠናቀቅ ሁለተኛውን የዕቅድ ዘመን ለመተግበር ጠንካራ ሕዝባዊ  ንቅናቄ በሚፈጠርበት  ወቅት በመሆኑ  ለህዝባዊ ተሳትፎና ለዕቅዱ  ቅድመ ዝግጅት እንቅስቃሴዎችን የሚያግዝ መሆኑን  አቶ ያለው  አመልክተዋል ።ባለፉት 21 ዓመታት  በህገ መንግሥቱ መሠረት የተገኙ የልማት ስኬቶች በብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ተሳትፎ  የተመዘገበ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ያለው  ዜጎች   በመልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲያዊ ግንባታ የሚደረገው  ተሳትፎ   ከጊዜ ወደ ጊዜ  እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል ።በፓናል ውይይቱ ከሁሉም ክልል አስተዳደሮች ፤የፌዴራልና የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች ፤ ከፍተኛ  የመንግሥት ሥራ ሃላፊዎች ፤ የክልሉ ዳያራስፖራዎችና  ተጋባዥ እንግዶች  በተገኙበት  በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ  ጠዋትና ከስዓት ውይይት እያደረጉ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል  ዘግቧል ።", "passage_id": "72dd98f9b04e1e5f9d5884c2397214ce" }, { "passage": "የፌዴራል ስርዓቱ የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን የእኩልነት፣ የሰላምና የልማት  ጥያቄዎችን  የመለሰና በቀደሙት ስርዓታት የነበሩ  ሌሎች  ስር የሰደዱ ችግሮችን መፍታቱን የፌዴራልና የአርብቶ አደር ልማት ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ።ሚኒስትሩ አቶ ካሳ ተክለብርሃን በተለይ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለጹት የፌዴራል ስርዓቱ  ቀጣይነት ያለው ልማትን ከማረጋገጥ፣ ዘላቂ ሰላምን ከማስፈንና የዴሞክራሲ ስርዓትን ከመገንባት አንጻር ባለፉት ሁለት  አስርት ዓመታት የጎላ ፋይዳ ነበረው።የሕዝቦች  የብሄር ጭቆናን አስወግዷል ፣ የሃይማኖት ነጻነትን አረጋግጧል፣ ሰላምና መረጋጋትን አስፍኗል፣   ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን አረጋግጧል፣ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን መሰረት እንዲይዝ አድርጓል ብለዋል።አገሪቱ በምስራቅ አፍሪካ የሰላም ደሴት እንድትሆን አስችላል ያሉት አቶ ካሳ አልፎ አልፎ የሚታዩ ትናንሽ ግጭቶች ቢኖሩም በመሰረታዊነት የአገራችን ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት የሚያውኩ አይደሉም ብለዋል።አቶ ካሳ አያይዘውም የህዝብ  የፖለቲካ ስልጣን ባለቤትነት ያረጋገጠ ስርዓት መገንባቱን ጠቁመው ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የአገሪቱ ዴሞክራሲ  እየተጠናከረ መምጣቱን ገልጸዋል።ሁሉም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ራሳቸውን በራሳቸው እንድያስተዳድሩና የአካባቢያቸውን ጸጋ ተጠቅመው አካባቢያቸውን እንዲያለሙ ቋንቋቸውንና ባህላችውን እንዲያበለጽጉ በማንነታቸው ኮርተው የጋራ አገራቸውን እንዲገነቡ የጎላ ሚና እንዳለው ም አቶ ካሳ ገልጸዋል።እንደ አቶ ካሳ ገለጻ ህዝቦች በአካባቢው ልማት፣ ዴሞክራሲ ግንባታና ሰላም በባለቤትነት ስሜት  በሰፊው እንዲሳተፍ አግዟል።  ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት የነበረው የጤና፣ ትምህርትና መሰረተ ልማት ዓለምን ባስደመመ መልክ መቀየሩም  የዚሁ   ውጤት መሆኑን አስምረውበታል።የፖለቲካ ስልጣን ባለቤት የሆኑት ሁሉም የአገሪቱ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የትምህርት ማዕድ ተቋዳሽ ለማድረግ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከ30 ሺሕ በላይ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም አቶ ካሳ ተናግረዋል።የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነት የኢትዮጵያ ፌዴራል ስርዓት ሁነኛ መለያ ነው ያሉት ሚኒስትሩ እያንዳንዱ አካባቢ ያለውን ጸጋ ለይቶ ልማትን ለማፋጠን እንዲተጋ አመች ሁኔታና አስተሳሰብ ፈጥሯል ብለዋል።  ከ40 በመቶ በላይ የሚሆኑ የዓለማችን አገራት የፌዴራል ስርዓት እንደሚከተሉ አስታውሰው የኢትዮጵያ ፌዴራል ስርዓት ብሔሮች፣ ብሔሰቦችና ሕዝቦች በቀጥታ የሚወከሉበትና ፍትሃዊነቱን ለማረጋገጥ ደግሞ በአንድ ሚሊዮን ህዝብ አንድ ተወካይ የሚሰይምበት   መሆኑ ከሌሎች አገራት ይለየዋል ብለዋል።የኢትዮጵያ ፌዴራል ስርዓት ማንነትን መሰረት ያደረገ አደረጃጀት በመያዙም ከሌሎች አገራት የፌዴራል ስርዓት መለየቱን ጠቁመው ይህ ቋንቋን ለመጠቀምና ባህልን ለማሳደግ የጎላ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል።የፌዴራል ስርዓቱን ፋይዳ ለሕብረተሰቡ በተለይ ለወጣቱ በማሳወቅ ደረጃ የተፈጠረው ክፍተት እንደ አንድ ተግዳሮች መውሰድ ይቻላል ያሉት ሚኒስተሩ በዚህ ምክንያት በሕገመንግስቱ የተመለሱ ጉዳዮች ላይ ጥያቄ ሲቀርብ ይስተዋላል ነው ያሉት።እኩል የመልማት እድል ለሁሉም ክልሎች ያጎናጸፈ ቢሆንም በሙያተኛ አቅምና በተነሳሽነት  ማነስ  የተነሳ ክልሎች በእኩል ደረጃ መልማት አለመቻላቸው ሌላው የስርዓቱ ተግዳሮት መሆኑን  ጠቁመው የመንግስት አካላት ስልጣንን ተገቢ ባልሆነ መንገድ መጠቀምም  ሌላው የጎላ ችግር እንደሆነ ገልጸዋል።አቶ ካሳ አያይዘውም የፌዴራል ስርዓቱ መሰረት በመገንባቱ፣ የአገሪቱ ሃብት እያደገ በመምጣቱ፣ በርካታ ዜጎች ከድህነት እየወጡ በመምጣታቸው፣ የማህበራዊ ተቋማት በመስፋፋት ላይ በመሆናቸውና ይህንን ተከትሎ የህዝብ ተጠቃሚነት እያደገ በመምጣቱ በፌዴራል ስርዓቱ የተደቀኑት ተግዳራቶችን ማስወገድ እንደሚቻል አስምረውበታል።", "passage_id": "c760550947d7b8aaba67a97a751dcbcc" }, { "passage": "የሚኒስትሮች ምክር ቤት በቅርቡ ባወጣው ደንብ የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሰላምና ልማት ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያን በማሻሻል፣ ተቋሙ የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ስትራቴጂ ጥናት ኢንስቲትዩት ተብሎ እንዲጠራና ትኩረቱም በውጭ ግንኙነት ላይ እንዲሆን አደረገ፡፡የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሰላምና ልማት ኢንስቲትዩት በ1988 ዓ.ም. የተመሠረተ ሲሆን፣ ላለፉት 20 ዓመታት የኢትዮጵያ መንግሥትን በሰላም፣ ፀጥታና ልማት ጉዳዮች ሲያማክር የቆየ ነው፡፡ በአገር አቀፍ እንዲሁም በአኅጉር ደረጃ የሚነሱ ግጭቶች አፈታት ዙሪያ አስተዋጽኦ ማድረግ፣ በእነዚሁ ጉዳዮች ላይ የአገር ውስጥ ችሎታና አቅምን በሥልጠና መገንባት፣ እንዲሁም በዲፕሎማሲ መስክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዲፕሎማቶችን በሥልጠና አቅማቸውን መገንባት በ1988 ዓ.ም. በወጣው ደንብ የተሰጠው ሥልጣን ነበር፡፡ፕሮፈሰር ክንፈ አብረሃ የመጀመሪያው የኢንስቲትዩቱ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ፣ ሕይወታቸው እስካለፈበት እ.ኤ.አ. 2007 ድረስ ድርጅቱን መርተዋል፡፡ የእሳቸውን ሕልፈት ተከትሎ ታዋቂው የሕወሓት መሥራች አባል አቶ ስበሃት ነጋ (አቦይ ስበሃት) ኢንስቲትዩቱን እንዲመሩ ተመድበዋል፡፡ በእሳቸው የኃላፊነት ዘመን ማለትም ከሁለት ዓመት በፊት ኢንስቲትዩቱ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር አለመግባባት ውስጥ ገብቶ ነበር፡፡ኢንስቲትዩቱ ተጠሪነቱ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመሆኑ የውጭ ጉዳይ ዲፕሎማቶችን የማሠልጠን ኃላፊነትም ተጥሎበታል፡፡ ይሁን እንጂ ተቋሙ የሥራ አፈጻጸሙን በተመለከተ ለውጭ ጉዳይ ሪፖርት እንደማያደርግና ዲፕሎማቶች የማሠልጠን ተልዕኮውን ባለመወጣቱ፣ ሚኒስቴሩ ማሠልጠኛ ለመክፈት መገደዱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቤቱታውን አቅርቦ ነበር፡፡ከአንድ ወር በፊት የፀደቀው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ማሻሻያ ደንብ ቁጥር 347/2008 የተቋሙ ተጠሪነት አሁንም ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲሆን በመወሰን፣ የሥራ ኃላፊነቱን ግን በአብዛኛው በኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩር አድርጓል፡፡“የአገሪቱን የውጭ ግንኙነትና አገራዊ ደኅንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ መሠረት በማድረግ የምርምር ሥራዎችን፣ ጉዳዮችን፣ የውይይትና የገለጻ መድረኮች በማከናወን አማራጭ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን በማፈላለግ ምክረ ሐሳብ ማቅረብ” ከኢንስቲትዩቱ ዋና ዓላማዎች መካከል አንዱ ነው፡፡የውጭ ግንኙነትና አገራዊ ደኅንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ፣ በአፈጻጸም በአጠቃላይ በዲፕሎማሲና በዳያስፖራ ጉዳዮች ላይ ጥናትና ምርምር በማድረግ አማራጭ የአፈጻጸም ሥልቶች ላይ ምክረ ሐሳብ የማቅረብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ቀደም ሲል ተቋሙ ከመንግሥት ድጎማ በተጨማሪ ከተለያዩ ለጋሾች በጀቱን ያገኝ ነበር፡፡ የማሻሻያ አዋጁ ግን የተቋሙ ሙሉ በጀት ከመንግሥት ብቻ እንዲሆን ወስኗል፡፡የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አሁንም አቶ ስበሃት ነጋ ናቸው፡፡", "passage_id": "5dd63a59a82de2064dd7679bd7edcdbe" } ]
5c60100317d4959308d299f96776eb61
d6886cef39a45f423e78f80aff975a26
ክልሉ የደን ሽፋኑን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
አዲሱ ገረመው አዲስ አበባ፡- የደቡብ ክልል በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚመጣውን ተግዳሮት ለመቀነስ ባደረገው አገራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የድርሻውን ለመወጣት እንዲችል የክልሉን የደን ሽፋን ከ23 በመቶ ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ::በተያዘው ዓመት 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ እንደሚዘጋጅ እና 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ችግኝ እንደሚተከልም ተጠቁሟል:: የደቡብ ክልል አካባቢ ጥበቃ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ቀቀቦ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በአንደኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አጠቃላይ የክልሉ የደን ሽፋን 19 በመቶ የነበረ ሲሆን፤ በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ደግሞ 25 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ በመሰራቱ 23 በመቶ ማድረስተችሏል::በቀጣይም እንደ አገር በሚደረገው ጥረት ውስጥ ክልሉ የሚጠበቅበትን ለማበርከት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሆን፤ በአስር ዓመት ውስጥም ሽፋኑን 30 በመቶ ለማድረስ ይሰራል   እንደ አቶ ሳሙኤል ገለጻ፤ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ የደን ሽፋንን ለማሳደግ በተደረገው ሰፊ ርብርብም ባለፈው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመን የደን ሽፋኑን 23 በመቶ ማድረስ ተችሏል::የደቡብ ክልል አጠቃላይ የደን ልማትን በተመለከተ ዋና ዓላማ ተደርጎ እየተሰራ ያለውም የክልሉን የደን ሽፋን ለማሳደግ ሲሆን፤ በዚህም መሰረት ከ2013 እስከ 2022 ዓ.ም በሚደረገው አጠቃላይ እንቅስቃሴ በየዓመቱ ዜሮ ነጥብ ሰባት በመቶ የደን ሽፋን በመጨመር የክልሉን ደን ሽፋን 30 በመቶ ለማድረስ ግብ ተቀምጦ እየተሰራ ነው::በዚህም የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስ በሚደረገው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ሥራ ክልሉ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው::ከዚህ አኳያ ክልሉ ባለፉት ሁለት ዓመታትም ይህንኑ መሠረት በማድረግ ሲሰራ ቆይቷል::በተለይ የአረንጓዴ አሻራ ስራን በተመለከተ በዋናነት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአንድ ጀምበር በርካታ ችግኞችን የመትከልና ሰፊ   አካባቢን በደን የመሸፈን ሥራ በትኩረት ተሰርቷል::በዚህም በ2011 ዓ.ም በአንድ ጀምበር 55 ሚሊዮን ችግኞችን፣ እንዲሁም በ2012 ዓ.ም 77 ሚሊዮን ችግኞችን መትከል ተችሏል::የደን ዘርፉ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በአካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ ያለውን ፋይዳ ከግምት በማስገባትም ነው በሚቀጥሉት አስር ዓመታት የደን ሽፋኑን 30 በመቶ ለማድረስ እየተሰራ ያለ መሆኑንም ነው አቶ ሳሙኤል የተናገሩት:: ግቡን ለማሳካት መጠነ ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን እና በዋናነት በየአካባቢው ያለውን የደን ሁኔታ የማጥናት ሥራ መከናወኑን የገለጹት አቶ ሳሙኤል፤ በተለይ በደቡብ ምዕራብ አካባቢ ያለውን የተፈጥሮ ደን የጥበቃ ሥራውን በከፍተኛ ደረጃ ለማጠናከርና ደኖች በሳሱባቸው አካባቢዎች መልሶ የመተካት ተግባራት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል::በማዕከላዊ ዞን አካባቢዎችም በተለይ ከፍተኛ የሆነ የደን ውድመት ያለበትና ከፍተኛ የሆነ የህዝብ መጨናነቅ ያለባቸው አካባቢዎች ላይ ለተለያዩ ዓላማዎች ሊውሉ የሚችሉ የችግኝ ተከላ ሥራም ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል:: ባለፈው ዓመት በአንድ ጀምበር ወደ 40ሺ ሄክታር መሬት በችግኝ መሸፈኑንና በተያዘው ዓመትም ወደ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኝ በማዘጋጀት 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ችግኝ እንደሚተከልም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል::ለዚህም የዛፍ ችግኝ ዝግጅት፣ ችግኝ ለማፍላት የሚያስችሉ ፕላስቲኮችን የማዘጋጀት፣ ችግኝ ጣቢያዎችን የማዘጋጀትና ሌሎችም ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰዋል::አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38395
[ { "passage": "በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 25 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ማቀዱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሐብት ቢሮ አስታወቀ፡፡የቢሮው  ኃላፊ አቶ ሺባባው ታረቀኝ ለዋልታ እንደገለፁት፤ ክልሉ ለተያዘው የመኸር ምርት ወቅት ካዘጋጀው 849 ሺህ ሄክታር መሬት ውስጥ እስካሁን 467 ሺህ ሄክታር መሬት በሰብል ለመሸፈን ተችሏል ፡፡በዘር ከተሸፈነው መሬት ከ25 ሚሊየን ኩንታል ምርት በላይ የሚጠበቅ ሲሆን ፤የጥራጥሬ ሰብሎች ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙና የቅባትና ዘይት እህሎች የዘር ወቅቱን ጠብቆ እንደሚከናወን አብራርተዋል ፡፡እንደ ኃላፊው ገለጻ 53ሺህ ኩንታል ማዳበሪያና ከ3ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ የበቆሎ ዘር አርሶአደሮቹ በሚፈልጉት መጠን ተከፋፍሏል፡፡በተያዘው ዓመት የማዳበሪያ ዋጋ መቀነሱን ተከትሎ የግብርና ግብዓት አቅርቦት በመጠኑ እንደጨመረም ጠቁመዋል ፡፡ለክልሉ አርሶአደሮች የግብርና ምርታማነትን ማጎልበት በሚቻልባቸው አማራጮች ላይ ተከታታይ ስልጠና መሰጠቱንም አቶ ሺባባው ገልጸዋል ፡፡", "passage_id": "6279274e591410abd7d39a18dc6bbb3b" }, { "passage": "አርባ ምንጭ፡- በ2011 ዓ.ም የክረምት ወቅት እና በሐምሌ 22 የአረንጓዴ አሻራ ቀን በደቡብ ክልል የተተከሉ ችግኞችን ለማህበረሰቡ በሰነድ ማስረከብ መቻሉ የፅድቀት ምጣኔውን ከፍ በማድረግ ውጤት ማስመዝገቡን ክልሉ አስታወቀ፡፡ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መለሰ መና ለአዲስ ዘመን እንደተናገሩት፣ ክልሉ በሁለቱ መርሐግብሮች የተተከሉ ችግኞችን በከተማ ለነዋሪዎች እንዲሁም ለመንግሥትና ለግል ተቋማት፣ በገጠር ደግሞ ለአርሶና አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ሰነድ አዘጋጅቶ አስረክቧል፡፡ ችግኞቹ ባለቤት እንዲኖራቸው በተሰራው ሥራ በአብዛኛው የክልሉ አካባቢዎች የሰነድ ርክክብ የተደረገ ሲሆን ፣በቀሩት ውስን አካባቢዎች ስራው እየተከናወነ ስለመሆኑም አቶ መለሰ አስረድተዋል፡፡ ከተከላ በስተጀርባ የሚከናወንን ተግባር ያለን ጥቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት በተከናወነው በዚህ ስራ ከዚህ ቀደም ይታይ የነበረውን ዝቅተኛ የፅድቀት ምጣኔ ማሻሻል መቻሉን የተናገሩት አቶ መለሰ፣ በዚህም እንደ ክልል በሁለቱ መርሐግብሮች የተተከሉ ችግኞች የፅድቀት ምጣኔ ከ85 በመቶ በላይ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ ይህ ሥራ ያስገኘው ውጤት ከፍተኛ በመሆኑ ተሞክሮውን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመቀመርና ወደ ሁሉም ክልሎች ለማስተላለፍ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን፣ ክልሉ በ2012 በጀት ዓመትም ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚሄድበት ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የግብርና ሚኒስቴር በሁለቱ መርሐ ግብሮች የተተከሉ ችግኞች ያሉበትን ሁኔታ ለሚዲያዎች ባስጎበኘበት ወቅት የዝግጅት ክፍላችን ባደረገው ምልከታ ችግኞቹ የተተከሉባቸው ቦታዎች ከእንስሳትና ሰዎች ንክኪ ነጻ ሆነው የእድገት ሁኔታቸውም በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገንዝቧል፡፡ ለአብነትም በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ወዜ ቀበሌ እና ጨንቻ ማረሚያ ቤትን ጨምሮ በወረዳው አንዳንድ አካባቢዎች እንዲሁም በወላይታ ዞን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ባደረግነው ምልከታ በተከላ ቦታዎቹ የጥበቃ ሠራተኞች ጭምር ተመድበው የአረምና ኩትኳቶ እንክብካቤ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በተለይም በወዜ ቀበሌ ከዚህ በፊት ምንም የደን ሽፋን ያልነበረውና በተደጋጋሚ በጎርፍ ይጠቃ የነበረ ተራራማ ቦታ አሁን ላይ በተተከሉ ችግኞች በማገገሙ ሸሽተው የነበሩ የዱር እንስሳት ጭምር እየተመለሱ ስለመሆኑ በጋሞ ዞን እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት መምሪያ የተፈጥሮ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፀጋየ ለታ ተናግረዋል፡፡ በደቡብ ክልል በ2012 በጀት ዓመት ከ400 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአፈርና ውሀ ጥበቃ ሥራ ለማከናወንና 4.8\nሚሊዮን በላይ ህዝብ ለማሳተፍ የታቀደ ሲሆን 1.3 ቢሊዮን ችግኝ ለማፍላት በአሁኑ ሰዓት 7 ሺህ የችግኝ ጣቢያዎች በመንግሥት፣ በአርሶአደሩ፣ በማህበረሰቡና በፕሮጀክቶች ድጋፍ መዘጋጀታቸው ተገልጿል፡፡ የክልሉ ዞኖችና ወረዳዎች ከጥር ወር አጋማሽ ጀምሮ ወደ ተግባር ለመግባት ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን የገለጹት አቶ መለሰ፣ ክልሉም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ማጠናቀቁን ገልፀዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 20/2012ድልነሳ ምንውየለት", "passage_id": "aa9b8a596e5fa3f0de3fe7e9d4c7e77c" }, { "passage": "አዲስ አበባ:- የዘንድሮው የአምስት ቢሊዮን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአገሪቱ በይፋ ከተጀመረ አንስቶ በአማራ ክልል ከአንድ ቢሊዮን 398\nሚሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።በቢሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው እንግዳየሁ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በዘንድሮው የአምስት ቢሊዮን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉ አንድ ነጥብ 58 ቢሊዮን የደረሱ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ ሲሆን፤ መርሃ ግብሩ በይፋ ከተጀመረ አንስቶ በክልሉ ከአንድ ቢሊዮን 398 ሚሊዮን 600ሺ በላይ ችግኞችን በመትከል ከወዲሁ የዕቅዱን 88 በመቶ ማሳካት ተችሏል።እንደ ዳይሬክተሩ ማብራሪያ፤ የዘንድሮው አገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በይፋ ከመጀመሩ አስቀድሞ በክልሉ የደን ልማት ስራ ላይ የሚስተዋሉ ደካማና ጠንካራ ጎኖች ተለይተው፤ ጥንካሬዎቹን በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ ለማድረግና ድክመቶቹን ለመቅረፍ የዳሰሳ ጥናቶች ተካሂደው ስትራቴጂክ ዶክመንት በማዘጋጀት አርሶ አደሩና ባለሙያው የጋራ መግባባት ላይ እንዲደረስ ውይይቶች ተካሂደዋል። በውይይቱ በደን ልማቱ እንደ ቁልፍ ችግር የተነሱት ከመጠን፣ ከመጽደቅ፣ የተተከሉ ችግኞች ባለቤት አልባ መሆን፣ የተተከሉ ችግኞችን ተከታትሎ መንከባከቡ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመሙላት፤ የተከላ ቦታዎች ተለይተው ተስማሚ የችግኝ ዝርያዎችን የማዘጋጀትና የችግኞቹን ባለቤት የመለየት ስራ ከመሰራቱ ባሻገር የተከላ ቦታዎች ምናባዊ እንዳይሆኑ በጂፒኤስ ድንበራቸው ተለይቶ በጂአይኤስ ፕሮግራም በአጠቃላይ የአጠቃቀም ካርታ እንዲዘጋጅላቸው መደረጉን ተናግረዋል።አቶ ጌታቸው ከነዚህ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በተጨማሪ የተለያዩ ግብዓቶችን በማሟላት በክልሉ ከአንድ ነጥብ 75 ቢሊዮን ችግኞች በላይ ማፍላት መቻሉን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ በዘንድሮው የአምስት ቢሊዮን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉ አንድ ነጥብ 58 ቢሊዮን ለተከላ የደረሱ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ ሲሆን፤ በአገሪቱ መርሃ ግብሩ በይፋ ከተጀመረ አንስቶ በክልሉ ከአንድ ቢሊዮን 398 ሚሊዮን 600ሺ በላይ ችግኞችን በመትከል ከወዲሁ የዕቅዱን 88 በመቶ ማሳካት መቻሉን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።አቶ ጌታቸው በክልሉ አንድ ነጥብ 58 ቢሊዮን ለተከላ የደረሱ ችግኞችን እስከ ነሃሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ተክሎ ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፤ በአብዛኛው አካባቢ በተሳካ ሁኔታ የችግኝ ተከላው ከወዲሁ መጠናቀቁን ጠቁመው፤ በዚህም በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉ 156ሺ 574 ሄክታር መሬት በችግኝ መሸፈኑን ተናግረዋል። በመጀመሪያው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉ ከተተከሉት ችግኞች ውስጥ 75 በመቶው መጽደቃቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመው፤ ዘንድሮ በአገር አቀፍ ደረጃ ለመትከል ከታቀደው ችግኝ አንጻር ክልሉ ለመትከል ያቀደው ቁጥር ያነሰው ችግኞችን ከመትከል ባሻገር መጽደቁ ላይ በትኩረት በመስራት ከተተከሉት ችግኞች 90 በመቶውን ለማጽደቅ ግልጽ የተጠያቂነት የአሰራር ስርዓት መዘርጋቱ መሆኑን ገልጸዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉ በአንድ ጀንበር ሃምሌ 9 ቀን 2012 ዓ.ም 190 ሚሊዮን 643 ሺ ችግኞች ሲተከሉ፤ ችግኝ በማፍላትና ችግኙን ከቦታ ቦታ በማጓጓዝ 24 ሺ ሰዎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ለማወቅ ተችሏል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 29/2012  ሶሎሞን በየነ", "passage_id": "52a187902c92fef5ba272dba52f97bdd" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል በዘንድሮ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ። የደቡብ ክልል የአካባቢ ጥበቃ፣ ደንና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ባለስልጣን እንደገለፀው፥ የዚህ ዓመት አገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ ቀን በቀጣዩ ሳምንት ግንቦት 28 ደቡብ ክልል ሀዋሳ ይጀመራል። የባለስልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ግዛቴ ግጄ እንዳሉት የተፈጥሮ አካባቢ ብክለትና ጉዳት ጉዳይ የማይመለከተው ስለሌለ እና የችግሩ ባለቤትም ማህበረሰቡ በመሆኑ መፍትሄውን ቆም ብሎ ሊያስብ ይገባል። እንደ ክልልም 1 ነጥብ 5 ቢሊየን የሚሆኑ ችግኞችን የመትከያ ቦታዎች የተዘጋጁ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፥ እስከ አሁን ባለው ሂደትም በክልሉ 50 ሚሊየን ችግኞች ተተክለዋል። በባለፈው አመት ከተተከሉት ችግኞች ውስጥም 84 በመቶ ያህሉ መጽደቃቸው ነው የተነገረው ። በሌላ በኩል የአለም አካባቢ ቀን ሀገር አቀፍ ፕሮግራም በዚህ አመት በአለም አቀፍ ደረጃ ለ47ኛ በሀገራችን ደግሞ “አካባቢን መጠበቅ የብዝሃ ህይወት ሀብትን መጠበቅ ነው” በሚል መሪ ቃል ለ27ኛ ጊዜ በደቡብ ክልል በተለያዩ ዝግጅቶች ታስቦ እንደሚውልም ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።", "passage_id": "4c705c8ef0637b3b49bdcdca711480bd" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- በኦሮሚያ ክልል ከዘንድሮው የመኸር እርሻ የሚገኘውን ምርት በ16 በመቶ ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ\nአቶ\nዳባ\nደበሌ\nትናንት\nበሰጡት\nመግለጫ፣\nበክልሉ\nባለፈው\nየምርት\nዘመን\nበዋና\nዋና\nሰብሎች\nየተገኘውን\n155 ሚሊዮን\nኩንታል\nምርት\nበዘንድሮው\nየምርት\nዘመን\nወደ\n186 ሚሊዮን\nኩንታል\nለማሳደግ\nመታቀዱን\nገልፀዋል፡፡\nእንደ\nእርሳቸው\nገለፃ፣\nበክልሉ\nእስካሁን\nድረስ\nያለው\nየምርት\nሥራ\nእንቅስቃሴ\nጥሩና\nየአየር\nሁኔታውም\nተስማሚ\nበመሆኑ\nከመቼውም\nጊዜ\nበበለጠ\nየተሻለ\nምርት\nይገኛል\nተብሎ\nይጠበቃል፡፡\nምርጥ\nዘርን\nጨምሮ\nበግብዓት\nአቅርቦትና\nስርጭት\nረገድ\nያሉ አንዳንድ ክፍተቶችን ለማስተካከል ሁለንተናዊ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህ ቀደም በብዛት ከውጭ ይገባ የነበረውን የቢራ ገብስ ባለፈው የምርት ዘመን በክልሉ ውስጥ በስፋት በማምረት ከውጭ ማስገባትን ማስቀረት እንዲሁም ከቢራና ከብቅል ፋብሪካዎች ጋር ስምምነት በማድረግ የገበያ ትስስር መፍጠር መቻሉን የጠቆሙት አቶ ዳባ፣ አሁን በክልሉ የሚመረተውን 28 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ወደ 37 ሚሊዮን ኩንታል በማሳደግ ከውጭ የሚገባውን የስንዴ ምርት ለመቀነስና በሂደትም ለማስቀረት መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ እቅዱን ለማሳካት ያግዝ ዘንድ ባለፈው ዓመት በትንሹ የተጀመረው ስንዴን በመስኖ የማምረት ሥራ ዘንድሮ በአራት ዞኖች በሚገኙ 18 ወረዳዎች እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል፡፡ አቶ ዳባ ‹‹አርሶ\nአደሩ ምርቱን በኅብረት\nሥራ ማኅበራት በኩል\nበማቅረብ በአርሶ አደሩና\nበሸማቹ መካከል ባሉ ደላላዎችና ሕገ-ወጥ ነጋዴዎች ምክንያት የሚደርስበትን ኪሳራ ለመቀነስ ከክልሉ የገበያ ኤጀንሲ ጋር በትብብር እየተሰራ ነው›› ብለዋል፡፡ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን አገር ውስጥ በማምረት መተካት፣ ወደ ውጭ ገበያ የሚላኩትን ምርቶች በዓይነት፣ በብዛትና በጥራት መጨመር፣ አጠቃላይ ምርትን በ16 በመቶ ማሳደግ፣ የቡናን አመራረት ዘመናዊ ማድረግ፣ ለአገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የሚሆን የስጋ ምርት በማቅረብ የእንስሳት ሀብት ልማትን ማሳደግና በጫት የግብይት ሰንሰለት ላይ ያለውን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውንም ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ እቅዱን ለማሳካት አርሶ አደሩ፣ ባለሙያውና በየደረጃው ያሉ አመራሮች ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባቸውም አቶ ዳባ አሳስበዋል፡፡አዲስ ዘመን ጳጉሜ 6/2011አንተነህ ቸሬ", "passage_id": "29d632e42c286b47a6ba865afb7c70c4" } ]
1dc01f2c6cb1b56a1f084167b866ee11
5e45edcdce70b2904a8207730751ec75
”ገበታ ለአገር” ፕሮጀክት አገራዊ የአንድነት ስሜት መፍጠሩን ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ ገለጹ
አዲስ አበባ፡- የገበታ ለአገር ፕሮጀክት እንደ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ አገራዊ የአንድነት ስሜት መፍጠሩን የሃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ ገለጹ። ኢዜአ በአካባቢ ጥበቃና ኢኮ ቱሪዝም ላይ የሚሰራውን በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝና በባለቤታቸው የተመሰረተውን የሃይለማሪያምና ሮማን ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚን አነጋግሯል። የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ የቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ በአገሪቷ በተፈጥሮ ብቻ የተገኙ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች መኖራቸውን ይናገራሉ። ወይዘሮ ሮማን ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የ”ገበታ ለአገር” ፕሮጀክት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የፈጠረውን አይነት አገራዊ የአንድነት ስሜት ፈጥሯል::ኢትዮጵያ ያሏት በርካታ የቱሪስት መስህቦችም የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ታሪካዊ አሻራ ያረፈባቸው፣ እምቅ ሀብትና ቅርሶችን ጭምር የያዙ በመሆናቸው እንደ “ገበታ ለአገር” አይነት ፕሮጀክቶች መጠናከር እንዳለባቸው ነው የተናገሩት። ወይዘሮ ሮማን፤ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷ ብቻ በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ገቢ ስለሚያመጣ ሀብቱን ጥቅም ላይ በማዋል ተጠቃሚ መሆን እንደሚቻልም አንስተዋል። በዚህም እንደ “ገበታ ለአገር” ያሉ ፕሮጀክቶችን አቅም በፈቀደ መጠን ማስፋት እንደሚገባና ሕዝቡም ለዚህ ድንቅ ዓላማ ድጋፍ በማድረግ የሚሳተፍበት መሆን እንዳለበት ነው የተናገሩት። ወይዘሮ ሮማን የ”ገበታ ለአገር” ፕሮጀክት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የፈጠረውን አይነት አገራዊ የአንድነት ስሜት መፍጠሩንም ገልጸዋል:: መረጃዎች እንደሚያመለክቱትም፤ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ሀብቷ ከአፍሪካ ግንባር ቀደም ከሆኑ አገሮች መካከል አንዷ ብትሆንም ከዘርፉ የሚጠበቀውን ያህል ጥቅም እያገኘች አይደለም። የቱሪስት መዳረሻዎችን በሚፈለገው ልክ ማስተዋወቅና ማልማት አለመቻሏ ደግሞ ለዘርፉ መቀጨጭ በምክንያትነት ይጠቀሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዘርፉ እንዲያንሰራራ ያደርጋል ያሉትን “ገበታ ለአገር” የተሰኘ ፕሮጀክት ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። በዚህም ትኩረት ተነፍጎት የቆየው የአገሪቷን የተፈጥሮ ሀብት የማልማት ስራ በጎርጎራ፣ በኮይሻና በወንጪ አካባቢዎች ለመስራት ታቅዶ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38398
[ { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 9፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የተፋሰሱን አገራት ፍትሃዊና የጋራ የተጠቃሚነት የሚያጠናከር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ገለፁ። “የታላቁ የህዳሴ ግድብ ቁልፍ ጉዳዮች፣ የወደፊት አገራዊ አቅጣጫና የዳያስፖራው ሚና” በሚል ርእስ በበይነ መረብ ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጨምሮ በናይል ተፋሰስ አገራት የሚገኙ የኢፌዲሪ አምባሳደሮች ተሳትፈዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ መላ ኢትዮጵያዊያን በራሳቸው ወጪ የሚገነቡት ፕሮጀክት በመሆኑ የመጀመሪያ ዓመት ዉሃ ሙሊት በተሳካ ሁኔታ በመከናወኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል አቶ ገዱ። ኢትዮጵያ ያላትን የውሃ ሀብት መጠቀም የሀገሪቱን ህልውና ልማት የማስጠበቅ ጉዳይ መሆኑንም አብራርተዋል። በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ በደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ሰብሳቢነት በሶስቱ አገራት መካከል የሚካሄደው ድርድር አበረታች ውጤት የታየበት መሆኑንም አንስተዋል። የናይል ተፋሰስ አገራትን የጋራ ተጠቃሚነት ለማሳካት የሚያስችለው የናይል ትብብር ማዕቀፍን ለመመስረት በአባል አገራቱ የተጀመረውን የትብብር ማዕቀፉን የማጽደቅ ሂደት በማጠናቀቅ ወደ ተግባር ማስገባት ወሳኝ መሆኑንም አቶ ገዱ ገልጸዋል። ሁሉም ኢትዮጰያዊያ ግድቡ እስኪጠናቀቅ ድረስ እስከዛሬ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል አምባሳደሮቹ የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጥሪ ማቅረባቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። መላ ኢትዮጵያዊያን በአገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት እንዲኖራቸውና የጋራ አቋም ለመያዝ መሰል መድረኮች ወሳኝ በመሆናቸው መጠናከር እንዳለባቸው በማሳሰብ የመድረኩን አዘጋጆችን አመስግነዋል። በውይይቱ በናይል ተፋሰስ አገራት የሚገኙ የኢፌዲሪ አምባሳደሮችና በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተደራዳሪ አባላት ውስጥ ኢንጅንር ጌዴዎን አስፋው፣ ዶክተር ያዕቆበ አርሳኖ፣ አቶ ዘሪሁን አበበ እንዲሁም ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ተሳትፈዋል።", "passage_id": "d13fa6935d8fd641337d8b840e4d1715" }, { "passage": "ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች የዲሞክራሲያዊ አንድነት መገለጫ መሆኑን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ኢትዮጵያውያን ያለምንም ብድርና እርዳታ በይቻላል መንፈስ ለዘመናት በአይደፈሬነት የቆየውን የአባይን ወንዝ በፍትሃዊነት ለመጠቀም የበኩላቸውን ያልተቋረጠ ድጋፍ በማድረግ አንድነታቸውን በተግባር ማረጋገጣቸውን ፅህፈት ቤቱ ለዋልታ በላቀው መግለጫ አመልክቷል፡፡በራስ አቅም እየተገነባ ለሚገኘው ግድብ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የአቅሙን ያህል ድጋፍ በማድረግ ግንባታው በተያዘለት ዕቅድ መዘረት እየተከናወነ እንደሚገኝ ፅህፈት ቤቱ አስረድቷል፡፡ በዚህም በድህነት ላይ ድልን ለመቀዳጀት ህዝቡ ቆርጦ መነሳቱን ገልጿል፡፡በተለይም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አገሪቱ የተለያዩ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ቢጋጥሟትም ህዝቡ ችግሮቹን በመቋቋምና በመከላከል ለግድቡ ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ አለሟቋረጡ አንስቷል፡፡በመግለጫው እንደተመለከተው የህዳሴው ግድብ ዋንጫ በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች በመዘዋወር ከፍተኛ ገቢ እያሰባሰበ ነው፡፡እስከ አሁንም በአምስት ክልሎች የተዘዋወረ ሲሆን በኦሮሚያ ክልል በሁሉም ዞኖችና ከተሞች ተዘዋውሮ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስገባቱ ለአብነት ጠቅሷል፡፡በክልሎች የታየው ርብርብ የዲሞክራሲያዊ አንድነቱ ተጨባጭ መገለጫ መሆኑን መግለጫው አስታውሶ ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ በመያያዝ ግዙፍ ልማቶችን ዕውን ለማድረግ ትግላቸውን ማጠናከራቸውን አስታውቋል፡፡ልማታዊ ርብርቡ ህዝቦች በድህትና ኋላቀርነት ላይ አንፀባራቂ ድሎችን በመጎናፀፍ የምግብ ዋስትናን እንዲያረጋግጡ ማስቻሉን ገልጿል ፡፡ህገ መንግስታዊ የፌዴራል ሥርዓቱ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ለአገራቸው ልማና ዕድገት በንቃት የሚሳተፉበትን ዕድል መፍጠሩንም እንዲሁ ፡፡11ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ትናንት በሐረር ከተማ ‹‹ህገ መንግስታችን ለዲሞክራሲያችንና ለአንድነታችን›› በሚል መሪ ቃል በታላቅ ድምቀት ተከብሯል፡፡\n ", "passage_id": "ba3c066864f28e6072360857b43d3827" }, { "passage": "በኢትዮጵያ የቆየውን የአብሮነትና የአንድነት እሴቶች ይበልጥ በማጠናከር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ወደ ፊት ማራመድ እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ተናገሩ።የሕብረ ብሔራዊ አንድነት ችቦ ከአዲስ አበባ ከተማ ወደ ጋምቤላ ክልል ሲገባ አቀባበል ተደርጎለታል።ርዕሰ መስተዳድሩ በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንዳሉት፣ የሕወሓት ጁንታ ሲያራምደው የነበረውን የከፋፋይ አስተሳሰብ በማስወገድ አንድነትንና አብሮነትን የመገንባቱ ተግባር ሊጠናከር ይገባል።የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች አንድነታቸውንና አብሮነታቸውን በማጠናከር የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ እና የብልጽግና ጉዞ ወደ ፊት ማራመድ እንዳለለባቸውም ተናግረዋል።የሕብረ ብሔራዊ አንድነት ችቦ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በቅብብሎሽ የብሔር ብሔረሰቦች በዓል እንዲከበር የተወሰነው በሕዝቦች መካከል ለዘመናት ጸንቶ የቆየውን አንድነት እና ወንድማማችነት ለማጠናከር መሆኑን አቶ ኡሞድ አስረድተዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወ/ሮ ዘርፈሸዋል ንጉሴ የሕብረ ብሔራዊ አንድነት ችቦውን ለጋምቤላ ክልል ሲያስረክቡ “ኢትዮጵያ ለሁሉም የምትበቃ ቤታችን፣ ከለላ እናታችን ናት” ብለዋል።በሀገሪቱ ሰላም፣ ዕድገት እና ብልጽግና  እንዲረጋገጥ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በአንድነት እና በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባም ተናግረዋል።የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች  በዓል ጁንታው ሀገር ለማፍረስ የከፈተው ዘመቻ በተቀለበሰበት ማግስት እየተከበረ መሆኑ የተለየ እንደሚያደረግው ጠቅሰዋል።የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አፈ -ጉባኤ አቶ ጁል ናጋል በበኩላቸው ባለፉት 27 ዓመታት ህዝቦችን ለመለያየት ሲሰበክ የነበረውን ከፋፋይ አስተሳሰብ በማስወገድና አንድነትን በማጠናከር የተጀመረው ልማት ለማስቀጠል በጋራ መረባረብ ይገባል ብለዋል።በሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ጭምር ታጅቦ ትናንት ጋምቤላ ከተማ የደረሰው  የህብር ብሄራዊ አንድነት ችቦ በክልሉ ከፍተኛ አመራሮች  እና የአካባቢው ነዋሪዎች አቀባበል የተደረገ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።", "passage_id": "17e7e4d69387a19212e89c883ec908c4" }, { "passage": "በአገሪቱ አኩሪ የሆነውንና ተዝቆ የማያልቅ የመቻቻል ፣ መተሳሰብና የአንድነት ፍቅር ይበልጥ  በማጎልበት አገሪቱ  የያዘችውን  የህዳሴ ጎዞ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ የኢፌዴሪ ጠቅላይ  ሚኒስትር  ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ።  ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ  በ12ኛው የብሔሮች ፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓልን በማስመልከት  በሰመራ ስታዲየም ተገኝተው ባደረጉት ንግግር  እንደገለጹት፤ በአገሪቱ  የቆየ ባህል የሆነውን የመተሳሰብ ፣ የመፈቃቀድና የአብሮነት ፍቅርን ይበልጥ በማጎልበት በአገሪቱ የተጀመረውን ጉዞ  አጠናክሮ  ለማስቀጠል እየተሠራ ነው ።ህዳር  29  የአገሪቱ  ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በማይናወጥ  የአንድነት መሠረት ላይ    እንዲቆሙ እንዲሁም የነጻነት ፣ እኩልነትና ዴሞክራሲያዊ  መብቶች እንዲጎናጸፉ ያስቻለውን  ታሪካዊ ዕለት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም አመልክተዋል ።እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር  ኃይለማርያም   ገለጻ ፤ ህዳር 29   በህዝቦች  መፈቃቀድ ላይ የተመሠረተ  አንድ የኢኮኖሚና ፖለቲካዊ ማህበረሰብ ለመፍጠር  ረጅሙን መንገድ  የጀመርንበት ልዩ ቀን ነው ።አገሪቷ የምትከተለው የፌደራላዊና ልማታዊ  ዴሞክራሲያዊ መሥመር አምርረው የሚጠሉ  ኃይሎች  የጋራ ግንባር እየፈጠሩ ሥርዓቱን ግብግብ እየፈጠሩ እንደሚገኙ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በወርቅ የተፈተነው መሥመር  ችግሩን በድል እየተወጣ ሲሆን የጠላት ኃይሎች  በራሳቸው ተደናቅፈው እየወደቁ ይገኛሉ ብለዋል ።አዲሲቷን ኢትዮጵያን ለመገንባት  የህዝባችንን   የልማትና ዴሞክራሲ ፍላጎት  በሟሟላት  ሥራውን  አጠናክሮ  በመቀጠል  ከትውልድ ትውልድ  በመቀባባል  የህዳሴውን ጉዞ ማሳካት እንደሚገባ  ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል ።ላለፉት  15 ዓመታት  በአገሪቱ  ባለሁለት  አሃዝ የኢኮኖሚ ዕድገት መመዝገቡ  በዓለም አቀፍ ድርጅቶች  ጭምር  ምስክርነት   የሠጡበት ጉዳይ  መሆኑን  ጠቅላይ ሚኒስትሩ  ጠቅሰዋል  ።ጥላቻና ጥራጣሬ  በየአጋጣሚው  ብቅ እያሉ የአገሪቱን የጋራ ግንባታ ለማስቆም የሚሹ ኃይሎች  እንዳሉ  የጠቆሙት  ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ይህን  እንቅፋት የአገር ግንባታውን  እንዳያስቆም መንግሥት ከህዝብ ጋር ተግቶ እንደሚሠራ  አስታውቀዋል ።በአገሪቱ  አንዳንድ አካባቢዎች  ግጭቶች  እንዳይከሰቱና ከተከሰቱም እንዲቆሙ ለማስቻል የፌደራል መንግሥት  ከክልሎች ጋር  በትብብር እየተሠራ መሆኑ የገለጹት  ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለግጭት መንስኤ የሆኑና ጥፋተኛ በሆኑ አካላት ላይ የማያዳግም  እርምጃ እንደሚወሰድ  አጽዕኖት አስገንዝበዋል ። ወጣቶች  መንግሥት  እየፈጠረ  ያለውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው በተለያዩ ዘርፎች ተጠቃሚ  እንዲሆኑ  ጠቅላይ  ሚኒሰትሩ ጥሪ አስተላልፈዋል ። 12ኛው   የብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች  በዓል “ በህገ መንግሥታችን የደመቀ  ህብረ ብሔራዊነታችን  ለህዳሲያችን ” በሚል መሪ ቃል በአፋር ብሔራዊ ክልል  ሰመራ ከተማ  በድምቀት እየተከበረ ይገኛል ።", "passage_id": "dcbc0371ac3340bda43931d8a91eef29" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሁሉም የኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት እንደመሆኑ መጠን ወደ ሥራ ገብቶ ለማየት የዘወ ትር ምኞታቸው መሆኑን አመለከቱ። በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን አባተ እንደተናገሩት፡- የአባይ ግድብ የኛ ጉዳይ ነው። ከጎረቤት ሀገር ጋር ሰላማዊ የሆነ ግንኙነት እንዲኖር ለማድረግ ካልሆነ በስተቀር የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን ነው መወሰን ያለበት። አሁን ላይ መንግሥት የያዘው አቋም ትክክለኛና አግባብነት ያለው በመሆኑ የውሃ ሙሌትም ጊዜውን ጠብቆ መሞላት አለበት እንጂ ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም ብለዋል። ኢትዮጵያ ህልውናዋን፤ ክብሯን፤ ነፃነቷን ለማስከበር በፍጹም አትደራደርም የሚሉት አቶ ሰለሞን፤ የራሳችን የሆነውን አባይ ገድበን ለመጠቀም የማንንም ፈቃድ መጠየቅ የለብንም። እስከአሁን ግብፅ ብቻዋን ስትጠቀም የነበረውን አባይ በጋራ ለመጠቀም የጋራ የሆነ የሚያግባቡ ሁኔታዎች ሲኖሩ ነው መደራደር የሚቻለው ካልሆነ በራሳችን ንብረት ወደኋላ የምንሸሽበት ምክንያት የለም። እኛ ኢትዮጵያውያን የሰውን ንብረት አንነ ካም የራሳችንን አሳልፈን አንሰጠም ሲሉ አቶ ሰለሞን ተናግረዋል። ኢትዮጵያውያን የጋራ ተጠቃሚ የሚያደርጉን ጉዳዮች እስካሉ ድረስ ከጎረቤትና ከውጭ ሀገራት ጋር ተግባብቶ የመኖር ባህል መሆኑን ጠቁመው፤ የአባይ ጉዳይ የኢትዮጵያ የልማትና የህልውና ጉዳይ ነው። ‹‹ግድቡ ሲጠናቀቅ ለልጅ ልጆቻችን ልማትና ተጠቃሚነትን በመስጠት ከድህነት የምንወጣበት አንዱ መንገዳችን ይሆናል›› ብለዋል። ለግድቡ መጠናቀቅ ከሌላው\nጊዜ በይበልጥ አንድነታችንና\nአብሮነታችንን በማስጠበቅ የጋራ\nርብርብ የሚጠይቅ ጉዳይ\nነው የሚሉት አቶ\nሰለሞን፤ ከሀገራችን ጎን\nበመቆም የውስጥና የውጭ\nሰላማችን እንዳይደፈርስ ጠብቀን\nዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ\nአብረን በመጓዝ ውሃው\nተሞልቶ ሥራ መጀመር እንዳለበት\nአመልክተዋል። ወይዘሮ መንበር መቋጫ በበኩላቸው፡- ግብፅ አባይ ብቻዋን ለዘመናት ስትጠቀም መቆየቷን የራሷን አድርጋ እንደትቆጥር ያደረጋት መሆኑን ጠቁመው፤ ግድቡ የኢትዮጵያውያን እንጂ የግብፅ ወይም የሌላ የውጭ ሀገር ንብረት አይደለም። የግድቡ ውሃ ሙሌት ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ ሳይሆን በቶሎ ውሃው ተሞልቶ ከውሃ ሀብታችን ተጠቃሚ የመሆን መብት እንዳለን መታወቅ አለበት ብለዋል። ‹‹ እኔ ባለኝ አቅም ከምንሠራው ትንሽ ሥራ አጠራቅሜ ቦንድ ገዝቻለሁ፤ የልጅ ልጄም ቦንድ እንዲገዛ አድርጌያለሁ›› የሚሉት ወይዘሮዋ፤ ከዚህም በላይ ለግድቡ ግንባታ የበኩላቸውን መወጣታቸውን ገልጸዋል። አባይ ህይወታችን መጦሪያ ቅርሳችን ነውም ብለዋል። እሳቸው የሚጦሩበት ልጆቻቸው የሚከብሩበት የአባይ ግድብ ተገድቦ ተጠቃሚ ለመሆን መጓጓታቸውን በመግለጽ፤ የግድቡ ሙሌት እውን እንዲሆን መንግሥት የያዘውን አቋም አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ህልውና ጉዳይ የሆነውን የግድቡን ውሃ መሌት ለማደናቀፍ በማሰብ በውጭ ገንዘብ ድጋፍ ኢትዮጵያን ለማተራመስ የሚጥሩ የውስጥም ሆነ የውጭ ኃይሎች መኖራቸ ውን ገልጸው፤ የግድቡ የልማት ሥራዎች በእነሱ ድርጊት የማይቋረጥ መሆኑን አውቀው አርፈው በመቀመጥ ከእኩይ ድርጊታቸው መቆጠብ እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ህዝቡ ሀገር ለማፍረስ የሚጥሩ ኃይሎች ምንም ጊዜ እንደማያንቀላፉ አውቆ ብልጥ በመሆን ለእነሱ ዕድሉን መስጠት የለብንም። ሁሉም ዜጋ ይህንን አውቆ የተሰማራበትን ሥራ ጠንክሮ በመሥራት ግድቡን ወደ ፊት ማስኬድ እንዳለበት አመልክተዋል። ከአባይ የምንጠብቀው ወጣቱ ትውልድ መስኖ እያለማ ሀገሩን በማበልጸግ የሥራ ዕድል የሚያገኝበት እንዲሆን ነውም ሲሉ ተናግረዋል። አባይ የሁላችንም አሻራ ያለበት ነው። ሁሉም ሰው የሚችለውን በማድረግ የተሳተፈበት በመሆኑ ግድቡን መድረስ ያለበት ቦታ ደርሶ እስከሚጠናቀቅ ድረስ እያንዳንዱ ዜጋ የሚጠበቅበትን መወጣት እንዳለበት ጠቁመዋል። ሁላችንም ተባብረን አባይን የእኛ ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል። ‹‹ ግድቡ ተጠናቅቆ ለኔም ደርሶ ይረዳኛል ብዬ ተስፋ አድርጋለሁ›› የሚሉት አቶ ኋሊት ከሊል በበኩላቸው፤አባይ የህልውናችን መሠረት በመሆኑ ማንም እንዳንገድብ ሊያደርገን አይገባም። ግድቡ ድሮም ለግብፅ እየፈሰሰ እኛ የምንሞገስበት ሀብታችን ቢሆንም፤ አሁንም ደግሞ ተገድቦልን እኛም ከግድባችን ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባን አመልክተዋል። ምንም\nእንኳን አባይ ለረጅም\nዘመናት ሳይገደብ በመኖሩ\nቢቆጩም ዛሬ ላይ\nተገድቦ ለማየት ተስፋ\nየጣሉበት በመሆኑ የግድብ\nየውሃ ሙሌት መጀመር\nእንዳለበት ጠቁመው፤ ህዳሴው\nግድብ ተጠናቆ ሥራ\nእስኪጀምር ድረስ ሁሉም\nያለውን አቅም ተጠቅሞ\nግድቡን እውን ለማድረግ\nመሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።አዲስ ዘመን ሀምሌ 14፣ 2012  በወርቅነሽ ደምሰው", "passage_id": "813251c63b364137cca3c13626b1fc2c" } ]
588ef73a8e2b622ad7d756be2818c328
2899e4ebddd8619f89f61acbd90b9325
የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በሕግ ማስከበር ሂደት ጉዳት የደረሰባቸው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ልዩ ሃይል አባላትን ጎበኙ
አዲስ አበባ፡- ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በሕግ ማስከበር ሂደት ጉዳት የደረሰባቸው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ልዩ ሃይል አባላትን ጎበኙ:: በጉብኝቱ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የአማራ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሙሉነሽ አበበን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው የምዕራብ እዝ መከላከያ ሆስፒታል እና የልዩ ሃይል የቁስለኞች ማቆያ በመገኘት በትግራይ ክልል በተደረገው የሕግ ማስከበር ሂደት ጉዳት የደረሰባቸውን የመከላከያ እና የአማራ ክልል ልዩ ሃይል አባላት በመጎብኘት አበረታተዋል::በሕግ ማስከበር ሀገራዊ ተልዕኮው ወቅት ለደረሰው የአካል ጉዳት ድጋፍ እንዲሆን ለሆስፒታሎቹ የዊልቸር፣ ክራንች እና ዎከር ድጋፍም ተደርጓል:: በተመሳሳይ በተያያዘ ዜናም በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው ጀግኖች እና ወላጆቻቸው በጦርነት መስዋት የሆኑባቸው የወታደር ልጆች ይኖሩበት የነበረውና የፈረሰውን የኢትዮጵያ የጀግኖች እና ህፃናት አምባን ለማቋቋም እየተሰራ መሆኑ ተጠቁሟል::ለሀገር የዋሉ ጀግኖች ማግኘት የሚገባቸውን ክብርና ትኩረት ወደጎን በማለት የኢትዮጵያ የጀግኖች እና ህፃናት አምባ ከለውጡ በፊት በነበረው ስርዓት አገልግሎት እንዲያቆም በመደረጉ በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው ጀግኖች እና ወላጆቻቸው በጦርነት መስዋት የሆኑባቸው የወታደር ልጆች ለሀገር ያበረከቱትን ውለታ የዘነጋ ተግባር ሲፈፀምባቸው ቆይቷል:: በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው ጀግኖች እና ወላጆቻቸው በጦርነት መስዋእት የሆኑባቸው የወታደር ልጆች ይኖሩበት የነበረውና የፈረሰውን የኢትዮጵያ የጀግኖች እና ህፃናት አምባን ለማቋቋም በበጎ ፈቃደኝነት የኢትዮጵያ የጀግኖች እና ህፃናት አምባ አደራጅ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ መግባቱን ብሔራዊ የጀግኖችና የሕፃናት አምባ በጎ አድራጎት ድርጅት የቦርድ ሊቀመንበር ዶክተር አዳሙ አንለይ ተናግረዋል:: የኢትዮጵያ የጀግኖች እና ህፃናት አምባ መቋቋም ለሀገር ክብር ዘብ በመቆም እስከ ህይወት መስዋዕትነት ለከፈሉና እየከፈሉ ላሉ ጀግኖችና ወላጆቻቸውን መስዋእት ላደረጉ የጀግኖች ልጆች ተገቢውን ቦታ እና ክብር መስጠት ያስችላል መባሉን የዘገበው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ነው::አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38401
[ { "passage": "በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እየተወሰደ ባለው የህግ ማስከበር ዕርምጃ በርካታ የታጠቁ ኃይሎች እጃቸውን ለጸጥታ ኃይሉ እየሰጡ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ ኃይል አስታወቀ።የህግ ማስከበርና የፀጥታውን ዘርፍ በበላይነት የሚመሩት ሌተናል ጀኔራል አስራት ዴኔሮ፤ የጥፋት ቡድኑ በመተከል ዞን በተለይም ቡለንና በቆጂ ወረዳዎች ዜጎችን በመግደል፣ ንብረት የመዝረፍና የማቃጠል አረመኔያዊ ተግባር መፈፀሙን አስታውሰዋል።የተጠናከረ ዘመቻ በማካሄድ በአካባቢው ህግ በማስከበር ሰላምን ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረት በርካታ የታጠቁ ኃይሎች እጃቸውን እየሰጡ መሆኑን ጠቅሰዋል።ታጣቂ ቡድኑ ቀደም ሲል የፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ስጋት አድሮባቸው መኖሪያቸውን ለቀው የነበሩ ዜጎችም ወደ ቀያቸው እየተመለሱ መሆኑን ሌተናል ጀኔራል አስራት ገልጸዋል።ግብረ ኃይሉ አካባቢውን ከተረከበ በኋላ በተለይ ስጋት ተፈጥሮባቸው የነበሩ አካባቢዎችን በማረጋጋት ወደ ተሻለ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ መደረጉን ተናግረዋል።በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪና የኮማንድ ፖስቱ የፖለቲካና ህዝባዊ ውይይቶች መሪ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ በዜጎች ላይ ጥቃት የፈፀመውን ታጣቂ ቡድን የማደን ሥራ መቀጠሉን ገልጸዋል።የተፈፀመውን ጥቃት በመምራትና በማስተ ባበር የተጠረጠሩና ጥቃቱን መከላከል ሲገባቸው ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ አመራሮች ላይ ህጋዊና ፖለቲካዊ ዕርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል።የጥፋት ቡድኑን ዓላማ ያልተቀበሉ የጉሙዝ ማህበረሰቦችን ጨምሮ በተለያዩ የማህበረሰብ አካላት ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወት ማጥፋት፣ አካል ማጉደልና ንብረት ማውደም መፈፀሙን አቶ ተስፋዬ ገልጸዋል።ችግሩ እኩይ ዓላማ\nያላቸው ኃይሎችን ብቻ\nየሚመለከት መሆኑን ጠቅሰው፤\n“በዘላቂነትመፍትሔ ለማበጀት ግብረ ኃይሉ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በቅንጅት እየሠራ ነው” ብለዋል።ለተፈናቀሉ ዜጎች ሰብአዊ ድጋፍ የማድረስና ወደ ቀዬአቸው መልሶ የማቋቋም ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አቶ ተስፋዬ ገልፀዋል።በሂደቱ የሰላምና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ህዝባዊ ውይይቶች እንደሚካሂዱም አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2013", "passage_id": "c906c640a35645044bc92f96bce009a4" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ታህሳስ 29 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የመከላከያ ሀይል ሰምሪት መምሪያ ኃላፊ ብ/ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው እንዳረጋገጡት 9 የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን 4 የቡድኑ አባላት ደግሞ እርምጃም ተወስዶባቸዋል።", "passage_id": "74f67d9ffd660f10bf82aba08fc7e272" }, { "passage": "በካማሼ ዞን ግጭት እጃቸው አለበት የተባሉ የፓሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ\\nየኦሮሚያ ፖሊስና መከላከያ ሁኔታውን ለማረጋጋት ሲሞክሩ የታጠቁ ኃይሎች ተኩስ በመክፈት ጉዳት አድርሰውባቸዋል ሲሉ የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳደርና ፀጥታ ሃላፊ አቶ ታከለ ነግረውናል።\n\nከጥቃቱ ጀርባ የታጠቁ ኃይሎች እንዳሉ ከቀያቸው የተፈናቀሉና በተለያየ ቦታ ተጠልለው የሚገኙ ግለሰቦች ለቢቢሲ ተናግረዋል።\n\n• በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የጤና ባለሙያዎች ጥቃት ደረሰባቸው\n\n• \"ማንም ቢሆን ኢትዮጵያን ለብቻዬ ሰራኋት ሊል አይቻለውም\" ጠ/ሚ ዐብይ\n\n• ሮናልዶ \"ደፍሮኛል\" ያለችው ሴት ከመብት ተሟጋቾች ድጋፍ አገኘች\n\nዘይነባ የተባሉት ከሳሲጋ የተፈናቀሉ ግለሰብ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን የታጠቁ ኃይሎች ተኩስ እንደከፈቱባቸውና ንብረታቸውን ጥለው እንደሸሹ ገልፀውልናል። \"አብራኝ ስትሸሽ የነበረችውን ጓደኛዬን በሚዘገንንና በሚያሰቅቅ ሁኔታ በስለት ተገድላለች \" ብለዋል። \n\nመከላከያ ኃይል አስር ታጣቂዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የገለፁት ኃላፊው እነዚህ በቁጥጥር ስር የዋሉ ኃይሎች የመኖሪያ ቤቶችን ሲያቃጥሉና ንብረት ሲያወድሙ በመታየታቸው እንደተያዙ አስረድተዋል።\n\nታጥቀው ተኩስ የከፈቱት ሃይሎች ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ልዩ ፖሊስ አባላት መሆናቸውንም አክለው ተናግረዋል። ግለሰቦቹ በቤኒሻንጉል ክልል በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ 8 በሚባለው ስፍራ እንደሚገኙም ጨምረው አስረድተዋል።\n\nበዚህ ጉዳይ ላይ ያነጋገርናቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል አስተዳደሪ አቶ አበራ ባየታ በዚህ ግጭት ፍፁም የክልሉ ኃይል አልተሳተፈም ሲሉ አስተባብለዋል። \n\nአክለውም የክልሉ ልዩ ኃይል በሎጅጋንፎይ ጮጌ ከተማ ላይ ነው ያለው ካሉ በኋላ በቁጥርም ምን ያህል እንደሆነ ይታወቃል ብለዋል። በተጨማሪም \"በፍፁም በጥቃት ላይ የተሰማራ የክልሉ ልዩ ኃይል የለንም\" በማለት ለምላሻቸው አፅንኦት ሰጥተውታል። \n\nእንዲህ ዓይነት ጥቃቶች እንዲፈፀም የሚያቀነነባብሩ አካላቶችን በማጣራት መንግሥት አስፈላጊውን ምርመራ በማካሄድ የህግ የበላይነትን ለማስከበር እየሰራ ነው ሲሉ የተናገሩት የምሥራቅ ወለጋ ዞን አስተዳደርና ፀጥታ ሃላፊ ሁኔታው አሁንም ሙሉ በሙሉ እንዳልቆመና የተፈናቃዮችም ቁጥር እየጨመረ እንደሆነ አስረድተዋል።\n\n", "passage_id": "0c5ce36936503144d86d6b4efc9f9691" }, { "passage": "ባሕር ዳር: ኅዳር 23/2013 (አብመድ) የአማራ ልዩ ኃይል አባላት የጁንታው ቡድን የራስ ምታት፣ የአማራ ህዝብ ዳግም ትንሳኤ አብሪ ኮከብ፣ የሰሜን ኢትዮጵያ ህግ የማስከበር እርምጃ ክስተት እና ለግፉአን ፈጥኖ ደራሽ እንደሆኑ በርካቶች ያለልዩነት መስክረዋል፡፡ የልዩ ኃይል አባላቱ ትህነግ ለለኮሰችው ጦርነት የዓመታት ዝግጅት እንዳደረገች ቢያውቁም ከጦርነት ድግስ ይልቅ የጦር ስልት፤ ከትጥቅ ይልቅ ልብ እንደሚያስፈልግ ስለሚያውቁ ባልተዘጋጁበት አውደ ውጊያ ሁሉ ግቡ ሲባሉ ገብተው ጠብ አጫሪዋን ድባቅ መቷት፡፡ከህግ ማስከበር ርምጃው ጎን ለጎን የክልሉን ሰላም በማስጠበቅ እና ከትህነግ አገዛዝ ነፃ በወጡ አካባቢዎች ማኅበረሰቡን በማረጋጋት፣ የቀሩ የትህነግ አባላትን በማፅዳት እና የፀጥታ ስጋት የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን አሁንም እየሰሩ ይገኛሉ፡፡የሰራዊቱ አባላትም የተሰማሩበትን ህግ የማስከበር ተልዕኮ በላቀ ብቃት እና ጀግንነት እንደተወጡ ገልጸው ህገወጥ ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ለፍርድ እስከሚቀርብ ድረስ ትግላችን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡ በአማራ ልዩ ኃይል የጣና ብርጌድ አባል የሆነችው ምክትል ሳጅን ዓለምነሽ ብርሃኔ ለህዝብ ነፃነት እና ለሃገር ሉአላዊነት ሲባል የጁንታዉ ቡድን ለፍርድ እስኪቀርብ ድረስ እና ህግ የማስከበሩ ተልዕኮ ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ የተሰጣትን ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን ነግራናለች፡፡ “ትግል እስከ ህይዎት መስዋዕትነት ድረስ ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን እናውቃለን፤ ብንሞት እንኳን የምንሞተው መሞት ለሚገባን ህዝብ በመሆኑ ደስ እያለን ታግለናል፣ እንታገላለንም” ብላለች ምክትል ሳጀን ዓለምነሽ፡፡ህግ የማስከበሩ ርምጃ ለኢትዮጵያዊያን የጋራ ጠላት በሆነው ህገወጥ ቡድን መክሰም ላይ ያነጣጠረ እንደነበርም ሃምሳ አለቃ ከድር አህመድ ነግሮናል፤ ለዚህም ግዳጃቸውን በአግባቡ እየተወጡ እንደሆነ አስረድቷል፡፡ “በርካታ ትግሎችን አልፈን የመጣን ነን፤ ወደፊትም ሃገር እና ህዝብ በፈለገን ግዳጅ ሁሉ ስኬታማ ሥራዎችን እንፈፅማለን” ነው ያለው፡፡በአማራ ልዩ ኃይል የጣና ብርጌድ ምክትል አዛዥ ኮማንደር አበራ ጌታሁን የልዩ ኃይል አባላቱ ከጂምሩ እስከ አሁን ድረስ የተሰጣቸውን ግዳጅ በብቃት እየፈፀሙ መሆኑን ተናግረዋል፤ የአማራ ህዝብ እና መንግስት ለልዩ ኃይል አባላቱ ከትጥቅ እስከ ስንቅ ያደረጉት ድጋፍ ትልቅ ጉልበት እንደሆናቸውም ኮማንደር አበራ አንስተዋል፤ ቀሪ ህግ የማስከበሩን ርምጃ በብቃት ለማጠናቀቅም ሰራዊቱ በሙሉ አቅሙ ዝግጁ እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡በራያ አካባቢም ህግ በማስከበር ተልዕኮው ውስጥ የየአካባቢው ማኅበረሰብ ለሰራዊቱ ላለው ቀና ድጋፍ እና ትብብር አባላቱ ምስጋና አቅርበዋል፡፡", "passage_id": "16db0eae993c7bf9836449a95d6f3d40" }, { "passage": "ከ600 በላይ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል መከላከል፣ ጸጥታና ህግ ማስከበር ዳይሬክቶሬት አመራሮችና አባላት ለሀገር ህልውና ሲሉ መስዋትነት ለከፈሉ የፌዴራል ፖሊስ አባላትና ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ክብር በመግለጽ የደም ልገሳ መርኃግብር አካሄዱ፡፡የጸጥታና ህግ ማስከበር ዳይሬክቶሬቱ የህወሓት ጽንፈኛ ቡድን በቁጥጥር ስር በማዋል ለህግ እንዲቀርቡ በሚደረገው ጥረት የፖሊሳዊ ግዴታቸውን ከመወጣት ጎን ለጎን ደም ከመለገስ ጀምሮ ማንኛውንም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ እንደሆኑ መናገራቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።", "passage_id": "ee06fb39022a9887c7d9d6cf6e99fd0f" } ]
66799b2cb8fcaf7220cf9e2a8095e68a
268d846e1bb036e0c358014447c76c8a
የቄራ ድርጅቶች አፈጻጸም 25 በመቶ ብቻ መሆኑ ተገለፀ
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ ሙሉ ሰርተፊኬት ወስደው ወደምርት የገቡት አስር የቄራ ድርጅቶች ማምረት ከሚችሉት ውስጥ 25 በመቶውን ብቻ እያመረቱ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።በግብርና ሚኒስቴር የኤክስፖርት ቄራዎች ድርጅት ሰርተፊኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ጌዲዮን ይልማ (ዶ/ር) በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፣ በሀገር ደረጃ ሰርተፊኬት ወስደው ወደሥራ የገቡ የቄራ ድርጅቶች 14 ቢሆኑም አራቱ በተለያዩ ምክንያቶች ሥራቸውን አቁመዋል።በሌላ በኩል በሥራ ላይ ያሉትም ቢሆኑ በአግባቡ እያመረቱ አይደለም ያሉት አቶ ጌዲዮን፣ በሥራ ላይ የሚገኙት አስሩ ቄራዎች ማምረት ከሚችሉት 25 በመቶ ብቻ እያመረቱ ይገኛሉ ብለዋል።እንደ ዶክተር ጌዲዮን ገለፃ የቄራ ድርጅቶቹ በሙሉ አቅማቸው ማምረት ያልቻሉት በገጠማቸው ውስጣዊ እና ውጫዊ ችግሮች ሲሆን ከነዚህም አንዱ የግብአት አቅርቦት ማነስ ነው።በተለይም ለእርድ የሚሆኑ እንስሳት በሚፈለገው ልክ አይቀርቡላቸውም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ይህም የሚከሰተው ከአቅርቦት ሰንሰለቱ፣ የኮንትሮባንድ፣ የውጪ ገበያ ትስስር ውስን መሆን እና የእርድ እንስሳት አቅርቦት ማነስ ከችግሮቹ መካከል ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን ገልፀዋል።ለዚህም ጉዳዩ የሚመለከታቸው እንደ ግብርና ሚኒስቴር፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ማህበራት እና የመሳሰሉት ተቋማት ተቀናጅተው እና ተናበው በሚፈለገው ልክ አለመስራታቸው ምክንያት መሆኑንም ጠቁመዋል። በዚህ የተነሳ ከዘርፉ የሚገኘውን ምርት ወደ ውጭ በመላክ ከዘርፉ ሊገኝ የሚገባው የውጭ ምንዛሪ በአግባቡ እንዳልተገኘ ጠቁመዋል። ድርጅቶቹ እስካሁን ድረስ ከመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት ስምምነት አድርገው የሚልኩት በሁለት ሀገሮች ብቻ በተንጠለጠለ የንግድ ሰንሰለት ስለሆነ የሚፈለገውን ገቢ ለማግኘት ይቸግራል ያሉት ዶክተር ጌዲዮን ይህም የማምረት አቅማቸውን ሙሉ በሙሉ እንዳይጠቀሙ ማነቆ እንደሆነና የተቀባይ ሀገሮች በየጊዜው መለዋወጥ እና የቅበላ መስፈርታቸው በየጊዜው መቀያየር ሌላው እንቅፋት እንደሆነ ገልጸዋል። በሌላ በኩልም በቋሚነት ለውጭ ገበያ ተብለው እንስሳት እየረቡ የሚቀርቡበት ሁኔታ ባለመኖሩ ከገበሬ እየተለቀመ እየተወሰደ የሚታረደው እንስሳ ለወደፊትም ሌላ አደጋ እንደሚያስከትል ጠቁመዋል። ችግሩን ለመቅረፍ በእንስሳት አቅርቦትና እንስሳት አቅራቢ ነጋዴዎችን አርብቶ አደሮችንና መሰል አካላትን ለማስተሳሰር በግብርና ሚኒስቴር በኩል ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ቢደረግም ውጤት አልተገኘም ብለዋል። ይህ እንዳይሆን ያደረገው ደግሞ በዘርፉ ውጤታማ ሥራ ለመስራት ተብለው የተቋቋሙ ባለድርሻ አካላት በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያለው የኢትዮጵያ ወተት ሥጋና ልማት ኢንስቲትዩት፣ ከግብርና ሚኒስቴር፣ ከቄራዎች፣ ከግል ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን መሬት ላይ የወረደ ሥራ በቅንጅት ባለመስራታቸው እንደሆነ ዶክተር ጌዲዮን ገልፀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 19/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38319
[ { "passage": "አዲስ አበባ ፣ መስከረም 20 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ሥር ያሉ 21 የልማት ድርጅቶች በ2012 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት 55 ነጥብ 55 ቢሊየን ብር አተረፉ፡፡ትርፉ በበጀት ዓመቱ ከተሰጠ የ300 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ምርትና አገልግሎት ሽያጭ የተገኘ መሆኑን የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ በየነ ገብረመስቀል ተናግረዋል፡፡በተጨማሪም 8 ነጥብ 67 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ምርትና አገልግሎታቸውን በውጭ ምንዛሪ ከሸጡ ድርጅቶች መገኘቱንም ነው የተናገሩት፡፡በተያዘው በጀት አመትም የልማት ድርጅቶቹ 376 ነጥብ 66 ቢሊየን ብር የምርትና አገልግሎት ሽያጭ ለማከናወንና ከታክስ በፊት 73 ነጥብ 81 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዷልም ነው ያሉት፡፡", "passage_id": "f46e0fda2e8fcab1264aa81c9d17dd55" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 18/2005 (ዋኢማ) – በአምስት ዓመቱ መርሃ ግብር በስኳር ልማት ተይዞ የነበረው ዕቅድ በተገቢው መልክ እየተፈጸመ መሆኑን የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን አስታወቀ።የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይ ፀሃዬ ለዋልታ እንደገለፁት በዕቅዱ 7 አዳዲስና 3 የማስፋፊያ አዳዲስ ፋብሪካዎችን ለመገንባት እቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን ሁለቱ የማስፋፊያ ፋብሪካዎች ተጠናቀዋል፤ ቀሪው ደግሞ በቀጣይ ዓመት ታህሳስ ወር ይጠናቀቃል።በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ የመጀመሪያ አመት በስራው አዲስነት የተነሳ የዝግጅት ጊዜ እንደነበር የገለጹት አቶ አባይ የፋብሪካዎቹ ዲዛይኖች ፤መሰረተ ልማት ፤ የሰው ሃይል ዝግጅት ፤ የኮንትራክተሮች ፍለጋና ስምምነት ስራዎች የተከናወኑባቸው እንደነበሩ አስታውሰዋል።ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ስራው በከፊል የተጀመረው በ2004 ዓ ም እንደነበርም ጠቁመዋል።በጣና በለስ ለሚገነቡ ሁለት ፋብሪካዎች የ50 ሺ ሄክታር የሸንኮራ አገዳ እርሻ ልማት የመስኖ መጥለፊያ ግንባታ የ31 ኪሎ ሜትር ቦይ ስራ መጠናቀቁን ገልጸው የመስኖ ውሃ መርጫ መሳሪያም ተገዝቶ ቱቦዎቹን መቅበር ተጀምሯልም ብለዋል።በኦሞ  ኩራዝም የ24 ኪሎ ሜትር ቦይ ስራ መጠናቀቁን ጠቁመው ጊዜያዊ የኦሞ ወንዝ መጥለፊያ ስራም ተሰርቷል ብለዋል።በወልቃይትና በጣና በለስ ተነሺዎች በተገቢው መንገድ እንዲሰፍሩ መደረጉን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ፤ አስፈላጊውን የትምህርት ፤ ጤና ፤ ስልጠና  እና  ውሃ የሚያገኙበት ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ግንባታም ተጠናቋል ብለዋል።በኩራዝ አንድ ፤ከሰም አንድ እና በጣና በለስ ሁለት በድምሩ አራት አዳዲስ ፋብሪካዎች ግንባታ ከ40 እስከ 50 በመቶ መድረሱን አቶ አባይ አስረድተዋል።በጥቅምት ወር ሁለቱ ፤ በታህሳስ ደግሞ አንዱ የማስፋፊያ ፋብሪካዎች ወደ ስራ እንደሚገቡ የገለጹት አቶ አባይ ሶስቱ ፋብሪካዎች በተሟላ መልክ ማምረት ሲጀምሩ የአገር ውስጥ ፍላጎት በአገር ምርት ይሸፈናል ብለዋል።መንግስት የስኳር እጥረትን ለማቃለል በየዓመቱ ከ2 ሚሊየን ኩንታል በላይ በውጭ ምንዛሪ እየገዛ የሚያስገባ ሲሆን በማስፋፊያ ፕሮግራሙ የተሰሩ ሶስት ትላልቅ ፋብሪካዎች ወደ ስራ ሲገቡ ይህንን ወጪ ማዳን እንደሚቻል ጠቁመዋል።የስኳር ልማት ፕሮጀክቶቹ በአብዛኛው በአገር ውስጥ አቅም የሚሰሩ በመሆኑ አገር በቀል ኮንትራክተሮች የበለጠ የሚጠቀሙበትና አቅማቸውን መገንባት የሚችሉበት ሁኔታ መፍጠር ተችሏልም ነው ያሉት።አቶ አባይ አያይዘውም ሰፈራ ከአካባቢው ህዝብና አስተዳደሮች ጋር በመመካከርና በመተማመን የሚሰራ በመሆኑ ውጤቱ ያማረ እየሆነ ነው ካሉ በኋላ በዚህ ረገድ ህዝብ ያለ ፍላጎቱ ተፈናቅሏል እያሉ መሰረተ ቢስ ወሬ የሚረጩ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች ከግል ጥቅማቸው ተነስተው መሆኑን ጠቁመዋል።የስኳር ልማት ፕሮጀክቶቹ እየተካሄዱ ያሉት ወደ ኋላ ቀርተው በነበሩ አከባቢዎች በመሆኑ የፋብሪካዎቹ መገንባት በአካባቢዎቹ ማህበራዊ ተቋማት እንዲሟሉና ከተሞች እንዲቆረቆሩ ምክንያት ሆነዋል ፤ የህዝቡም አኗኗር እየተሻሻለ መጥቷል ብለዋል።", "passage_id": "e9f0e755de181aab9227f7b0edbca5d4" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ባላቸው ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ ሂደት በተቀመጠላቸው ጊዜና በጀት ባለመጠናቀቃቸው ምክንያት በአማካይ እስከ 107 በመቶ የደረሰ የወጪ ጭማሪ ማስከተላቸው ተገለፀ። የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን በተመረጡ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ ያደረገውን የአፈፃፀም ግምገማ ጥናት ለባለድርሻዎች ትናንት አቅርቧል።በግምገማው ውጤት ውይይት ወቅት የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የኮሚሽነሩ ልዩ አማካሪ አቶ መለሰ ተገኘ እንደተናገሩት፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮንስትራክሽን ዘርፉ በተነፃፃሪነት ከፍተኛ በጀት የሚመደብለት ሲሆን፤ መንግሥታት ለዘርፉ ከሚመድቡት በጀት ውስጥ ከ15 እስከ 30 በመቶ የሚሆነው በሙስና ሊባክን እንደሚችል መረጃዎች ያሳያሉ። ይህ ደግሞ ዘርፉ ለሙስና ተጋላጭ መሆኑን ያመለክታል። የኢትዮጵያ መንግሥትም ከዓመታዊ በጀቱ ውስጥ ለግዢው ዘርፍ ከሚመድበው 60 በመቶ ውስጥ 70 በመቶው ለኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚወጣ ነው።ይሄን መነሻ በማድረግም ኮሚሽኑ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የስኳር ኮርፖሬሽን፣ የኤሌክትሪክ ሃይል፣ የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣንና የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን እያስገነቧቸው ባሏቸው ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ የፕሮጀክት አፈፃፀም ግምገማ ጥናት ያካሄደ ሲሆን፤ በዚህም ፕሮጀክቶች በጊዜም ሆነ በገንዘብ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየታቸው ተስተውሏል። ለአብነት ኮስት ኢትዮጵያ ያከናወነው ጥናት እንዳመለከተው አጠቃላይ የግንባታ ዘርፉ ያለው አማካይ ዋጋ ጭማሪ 107 በመቶ ይደርሳል።የኮሚሽኑን የግምገማ ጥናት ያቀረቡት አቶ ኪዳነ ምህረት፣ አቶ ሰይፈዲን ኪያር እና አቶ ወንድይራድ ሰይፉ በበኩላቸው እንደገለፁት፤ ጥናቱ በ17 ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ የተከናወነ ሲሆን፤ ከተጠናቀቁት 12 የግምገማ ጥናቶች ውስጥ አምስቱ (ያዩ ዩሪያ ማዳበሪያ ኮምፕሌክስ ግንባታ፣ ጋሸና-ላሊበላ-ሰቆጣ መንገድ ግንባታ፣ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያ ሆስፒታል ግንባታ፣ የአራራት ሆቴል ኮተቤ ኮሌጅ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እና የሐረማያ ቲቺንግ ሆስፒታል) እንዲቀርቡ ሆኗል። በግምገማ ጥናቱ መለየት እንደተቻለውም ፕሮጀክቶች በተለያየ ምክንያት በተቀመጠላቸው ጊዜና በጀት እየተጠናቀቁ ባለመሆናቸው አንድም ለህዝቡ አገልግሎት እንዳይሰጡ ሆኗል፤ ሁለተኛም መንግሥትን ላልተገባ ወጪ እየዳረጉት፣ ለሙስናና ለብልሹ አሠራርም በር እየከፈቱ ይገኛል።አቅራቢዎቹ በግምገማ ጥናቱ ካቀረቧቸው መካከል ጋሸና-ላሊበላ-ሰቆጣ መንገድ ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን፤ ይህ ፕሮጀክት ከ2 ነጥብ 04 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚከናወን የ99 ነጥብ 75 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ ነው። ለፕሮጀክቱ አራት ጊዜ የጨረታ ማስተካከያ የተደረገ በመሆኑ ለሙስናና ብልሹ በር የሚከፍትና በተረታ ተወዳዳሪዎች ላይ ተጽዕኖ ያሳደረ ሆኖ ታይቷል። ግልፅ የመወዳደሪያ መስፈርትም አልነበረውም። የውጭ ምንዛሬ ብክነት እንዲከሰት አድርጓል። በዲዛይን ለውጥ ምክንያትም ወደ 49 ሚሊየን ብር ለኮንትራክተሩ እንዲከፈል ሆኗል። በተመሳሳይ 875 ሚሊየን 77 ሺ 561 ብር ሰኔ 2006 ዓ.ም ውል ተገብቶለት በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይጠበቅ የነበረው አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቲቺንግ ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ ፕሮጀክት፤ ዛሬም ድረስ ከወሰን ማስከበር፣ ተደጋጋሚ የዲዛይን ለውጥና ሌሎች ምክንያቶች ጋር ተዳምሮ እስከ ጥር 2011 ዓ.ም ድረስ አፈፃፀሙ ከ61 በመቶ መዝለል ባለመቻሉ ተጨማሪ 84 ሚሊየን ብር እንዲከፈል አድርጓል። አሁን ላይ የማጠናቀቂያ ወጪው ወደ አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር እንዲደርስ አድርጎታል። ከዚህ ባለፈ የፕሮጀክቱ በጀት በጨረታ ኮሚቴ የቀረበውን የ875 ሚሊየን ሰባት ሺህ 561 ብር ዋጋ በኮንትራት ፊርማ ወቅት ባልታወቀ ምክንያት 70 ሺ ብር በመጨመር 875 ሚሊየን 77 ሺ 561 ብር ተቀይሯል።እንደ ጥናት አቅራቢዎቹ ገለፃ፤ በጥናቱ እንደተለየው በጊዜም በበጀትም ያልተገባ ጭማሪ መስተዋሉ ሲሆን፤ ይሄም ለሌሎች ፕሮጀክቶች መዋል የሚገባውን ፋይናንስ በመውሰድም በመንግሥት ላይም ጫና እያሳደሩ ይገኛል። በመሆኑም ፕሮጀክቶቹ በህዝብ ሀብት የሚከናወኑ እንደመሆናቸው በአግባቡ ተፈትሸው ውል ሊታደስላቸውና በአግባቡ ተገንብተው እንዲጠናቀቁ የሚያስችል በጥናት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ሊሰጣቸውና የህዝብን ሀብት ከብክነት መታደግ፤ ፕሮጀክቶቹም ወደ አገልግሎት እንዲገቡ ማድረግ ይገባል። ቀጣይ የሚከናወኑ ታላላቅ ፕሮጀክቶችም አጠቃላይ ሂደታቸው ለህዝቡ ግልፅ የሚሆንበት ዕድል ሊፈጠር፤ ውድድርን መሰረት ያደረገ የግንባታ ጨረታን መከተል፤ ተጠያቂነትን ማስፈን፤ ዋጋ፣ ጊዜና ጥራትን ማዕከል ያደረጉ ሥራዎች እንዲከናወኑ ማስቻል ያስፈልጋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2012 ወንድወሰን ሽመልስ", "passage_id": "3a83f1b95a9f23d48672adc2c8d68be4" }, { "passage": "አየር መንገድና ንግድ ባንክ 83 በመቶ አመንጭተዋልከተሸጡ ድርጅቶች 2.1 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰብስቧልየመንግሥት የልማት ድርጅቶች በ2012 ዓ.ም. አፈጻጸማቸው ከ300 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ከማስገኘታቸው በተጨማሪ፣ ምርትና አገልግሎታቸውን በውጭ ምንዛሪ ከሚሸጡ ድርጅቶች 8.67 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱ ተገለጸ፡፡ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ በየነ ገብረ መስቀል መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት እንዳስታወቁት፣ በ2012 ዓ.ም. በውጭ ምንዛሪ እንደሚገኝ ከሚጠበቀው 12.52 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 8.67 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል፡፡ ለዚህ ገቢ መገኘት የኢትዮጵያ አየር መንገድና የኢትየጵያ ንግድ ባንክ 83 በመቶውን በመያዝ ትልቅ ድርሻ ነበራቸው ብለዋል፡፡ እንደ ኤጀንሲው መግለጫ አየር መንገዱ 3.75 ቢሊዮን ዶላር በማስገኘት የ43.2 በመቶ ድርሻ ሲይዝ፣ ንግድ ባንክ በበኩሉ 3.44 ቢሊዮን ዶላር በማስገኘት የ40 በመቶ ገደማ ድርሻ ወስዷል፡፡ በተሸኘው ዓመት ከ21 የልማት ድርጅቶች ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው ጠቅላላ የገቢ መጠን ከ338 ቢሊዮን ብር በላይ ነበር ያሉት አቶ በየነ፣ ከታቀደው ገቢ 89 በመቶ መሳካቱንና 300.5 ቢሊዮን ብር መገኘቱን ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ ገቢ ውስጥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ122 ቢሊዮን ብር ማስገኘቱ ቀደም ብሎ ሲገለጽ፣ ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ከ47.7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስገባቱ ታውቋል፡፡ በትርፍ ረገድ ኢትዮ ቴሌኮም ከ28 ቢሊዮን ብር በላይ ማስመዝገቡም ተጠቅሷል፡፡ በጠቅላላው ከ21 የልማት ድርጅቶች እንቅስቃሴ ይጠበቅ የነበረው የትርፍ መጠን ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ቢሆንም፣ በውጤቱ 56 ቢሊዮን ብር ያህል ተመዝግቧል፡፡ ከታቀደው የትርፍ መጠን 79 በመቶው ተሳክቷል፡፡ በዚህ መሠረት ለመንግሥት የትርፍ ድርሻ ክፍያ በመፈጸም ረገድ ንግድ ባንክ ስምንት ቢሊዮን ብር ገቢ ሲያደርግ፣ ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ከ4.5 ቢሊዮን ብር በላይ ማስገባቱን አቶ በየነ አስታውቀዋል፡፡ ይሁን እንጂ ለኤጀንሲው ተጠሪ ከሆኑና የትርፍ ድርሻ ክፍያ መፈጸም ከሚጠበቅባቸው ድርጅቶች ይጠበቅ የነበረው ክፍያ ከ19 ቢሊዮን ብር በላይ ነበር፡፡ ድርጅቶቹ ያለባቸውን የአገር ውስጥና የውጭ ዕዳ ከመክፈል አኳያም አፈጻጸማቸው ታይቷል፡፡ 16.9 ቢሊዮን ብር የአገር ውስጥ ዕዳ እንዲከፍሉ ታቅዶ፣ 15.3 ቢሊዮን ብር ክፍያ መፈጸማቸው ተገልጿል፡፡ በውጭ ዕዳ ረገድ 604 ሚሊዮን ዶላር መክፈላቸው ተጠቅሷል፡፡ ከዘህ ውስጥ ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ በኢትዮ ቴሌኮም የተከፈለ ነው፡፡ የመንግሥት ይዞታ ሥር የነበሩና ወደ ግል ከተዛወሩ የልማት ድርጅቶች ሽያጭ መከፈል የነበረበትና ሳይከፈል በመቆየቱ በቅጣትና ወለድ ታሳቢ ቢደረግም፣ በኮሮና ተፅዕኖ ምክንያት ለሌሎች ድርጅቶች የተደረገው የወለድና ቅጣት የማንሳት ምሕረት፣ እነዚህን ድርጅቶችም ለገዙ ኩባንያዎች ታሳቢ ተድርጓል፡፡ በዚህ መሠረት ኤጀንሲው እንዲከፈል የሚጠብቀው 3.3 ቢሊዮን ብር ሲሆን፣ በ2012 ዓ.ም. 330 ሚሊዮን ብር ገቢ እንደተደረገ፣ በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት ውስጥ 1.8 ቢሊዮን ብር ክፍያ በማግኘቱ በጠቅላላው የ2.1 ቢሊዮን ብር ክፍያ እንደተፈጸመለት አስታውቋል፡፡ ይህ ገንዘብ ከተሸጡ ድርጅቶች እንዲከፈል ከሚጠበቀው 60 በመቶ የሚሸፍን ነው፡፡ 1.2 ቢሊዮን ብር ያልተሰበሰበ ቀሪ ክፍያ እንደሚቀረው ኤጀንሲው አስታውቋል፡፡ ከዚህ ባሻገር በ2013 ዓ.ም. ኤጀንሲው ከሚያስተዳድራቸው ድርጅቶች 376.6 ቢሊዮን ብር ገቢ እንደሚጠበቅ አቶ በየነ ገልጸዋል፡፡ በ2012 ዓ.ም. ከተገኘው የ22 በመቶ ጭማሪ ተደርጎበታል፡፡ በትርፍ ረገድም የ36 በመቶ ጭማሪ የታከለበት 74 ቢሊዮን ብር ገደማ ከታክስ በፊት ትርፍ እንደሚገኝ ይጠበቃል፡፡ በውጭ ምንዛሪ ላይ ካለፈው የ14 በመቶ ቅናሽ የተደረገበት 7.5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መታቀዱ ታውቋል፡፡ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ በአሁኑ ወቅት 21 ድርጅቶች በሥሩ እያስተዳደረ ሲሆን፣ በ2012 ዓ.ም. 20ዎቹም አትራፊ ሆነው ዓመቱን ማጠናቀቃቸውን ዋና ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል፡፡ ብቸኛው ኪሳራ የደረሰበት የልማት ድርጅት ስኳር ኮርፖሬሽን ሆኗል፡፡ በዚህ ዓመት እንቅስቃሴ 71.5 ቢሊዮን ብር ኢንቨስት ለማድረግ መታቀዱ ሲጠቀስ፣ አብዛኛው ወይም 98 በመቶው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርሻ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በዓመቱ 11 ድርጅቶች ወደ ግል እንደሚዛወሩ ሲገለጽ፣ አብዛኞቹም የስኳር ፋብሪካዎች እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡   ", "passage_id": "2504f45ae71efdc45f3e13eda6803705" }, { "passage": "በዘንድሮ የበጀት ዓመት ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ ከተደረጉት 50 አይነት መድሓኒቶች ውስጥ 8 የሚሆኑት ጥቅም ላይ እንዳይውሉ መደረጉን የኢትዮጵያ የምግብ ፣ መድሓኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታወቀ ።የባለሥልጣኑ የጤና ተቋማት ኢንስፔክሽን ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ እንዳለ ለዋልታ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ባለፉት 9 ወራት በውጭ ተመርተው ወደ አገር ውስጥ ከገቡት መድሓኒቶች ውስጥ 8 የሚሆኑት በድህረ  ገበያ ቅኝት ተገምግመው የአገሪቱን  መስፈርት ባለሟሟላታቸው ምክንያት ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ተደርጓል ብለዋል ።ባለሥልጣኑ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ መድሓኒቶችን በውጭ አገር የአመራረቱን ሂደት በማየት ፣በመግቢያና በመውጫ ኬላዎች የመቆጣጣር ሥራዎችንበማካሄድ  እንዲሁም በገበያ ላይ እያሉ ጥናት በማድረግ የአገሪቱን የመድሓኒት ጥራት ስለሟሟለታቸው ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያድረግ አቶ ገዛኸኝ አስረድተዋል ።መድሓኒቶች ወደ አገር ውስጥ የሚገቡት በሞጆ ደረቅ ወደብ ፣ በአደማና በቃሊቲ ጉምሩክ ጣቢያ ብቻ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ገዛኸኝ በህገወጥ መልኩ የሚገቡትን መድሓኒቶች ለመከላከል በኬላዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል ።ባለሥልጣኑ የተለያዩ የአገሪቱ ተቋማት ትክክለኛ መድሓኒቶች ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲውሉ ለማድረግ የቁጥጥር ሥራዎች ያካሄዳል ያሉት አቶ ገዛኸኝ በዘንድሮ የበጀት ዓመት  5  ሚሊዮን ብር የሚያወጡና መስፈርት የሟያሟሉ መድሓኒቶች ተገኝተው እርምጃ እንዲወሰድ መደረጉን ገልጸዋል ።በተለይ የኢትዮጵያ መድሃኒት ፈንድ አቅርቦት አጄንሲ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲውል የሚገዛቸው መድሓኒቶች በአግባቡ ለህብረተሰብ አገልግሎት መዋላቸውን ለማረጋገጥ በሆስፒታሎች ፣ በጤና ጣቢያዎችና ኬላዎች በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋላቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል  የፋርማሲ ሶፍትዌር ተዘጋጅቶ ሥራ ላይ ውሏል ።ኢትዮጵያ በአጠቃላይ 82 በመቶ የሚሆነውን የመድሐኒት ፍላጎቷን የምትሸፍነው ከውጭ በሚገባው የመድሓኒት ምርት ሲሆን ቀሪው 18 በመቶ የሚሆነው በአገር ውስጥ በፋብሪካዎች ምርት የሚሸፈን ነው ።              ", "passage_id": "03c57ac51eabea57886b14f965ea5fbe" } ]
30f780a64e5b9bfe19c1086081c65244
49207beb36578f8e119afcf5b99b9427
በአሶሳ ከተማ ከ552 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ሕገ-ወጥ የትምባሆ ምርቶች ተያዙ
አዲስ አበባ፡- በአሶሳ ከተማ በትምባሆ ምርቶች ላይ የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማከናወን ከ552 ሺህ 750 ብር በላይ የሚገመት ሕገ-ወጥ የተለያዩ የትምባሆ ምርቶች መያዛቸውን የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡ባለሥልጣኑ እንዳስታወቀው፤ በጸጥታ እና በባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ክትትልና ቁጥጥር በአሶሳ ከተማ በትምባሆ ምርቶች ላይ የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማከናወን ከ552 ሺህ 750 ብር በላይ የሚገመት ሕገ-ወጥ የተለያዩ የትምባሆ ምርቶች ተይዘዋል፡፡በደቡብ ምዕራብ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አስተባባሪነት ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ተቆጣጣሪዎች ከአሶሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ተቆጣጣሪዎች እና ከከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አባሎች ጋር በመቀናጀት ባከናወነው ኦፕሬሽን ሥራ የትንባሆ ምርቶቹ መያዛቸውን ከኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 19/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38316
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን አጋርፋ ወረዳ ሰሞኑን በተከሰተው ሁከትና ግርግር አጥፊዎች ሲጠቀሙባቸው የነበሩ የጦር መሣሪያዎች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ።በባሌ ዞን ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ተስፋዬ ከበደ እንደገለጹት÷ በወረዳው ለጥፋት የተንቀሳቀሰው ቡድን ሲገለገልባቸው የነበሩ የጦር መሣሪያዎች ተይዘዋል።ከነዚህም ዘጠኝ ሽጉጦች፣ አራት ክላሽንኮቭ ጠብ መንጃዎች እና በቁጥር 434 የሚሆኑ ተቀጣጣይ የፈንጂ ገመዶች ይገኙበታል፡፡በተከሰተው ሁከትና ግርግር በወረዳው ኅብረተሰቡ ሲገለገልባቸው የነበሩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣ በወረዳው የ64 አባወራ መኖሪያ ቤቶች ሲወድሙ በዚህም ከ1ሺህ 200 በላይ ዜጎች መፈናቀላቸውን ኮማንደሩ አስታውቀዋል፡፡እንዲሁም በፖሊስ ጣቢያና ኅብረተሰቡ በሚገለገልበት ድልድይ ላይ ተጠምዶ የነበረ ተቀጣጣይ ፈንጂ የጸጥታ ኃይሎች ማክሸፋቸውን አስረድተዋል፡፡በወረዳው በሁከት ፈጣሪዎች በርካታ ወንጀሎች መፈጸማቸውን የገለጹት ኃላፊው፤ የነፍስ ማጥፋት፣ ዘረፋና የቤትና የንብረት ቃጠሎ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡በሌላ በኩል ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የተዘረፉ 101 የሚሆኑ የጦር መሣሪያዎች፣ ከመሥሪያ ቤቶቹ የተዘረፈ ንብረት እና ከአርሶ አደር የተዘረፉ 85 የቀንድ ከብቶችም መመለሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡", "passage_id": "37f4cc3da3b94076d956b48829492842" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከ16 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ ገቢና ወጪ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ባለፉት ሰባት ቀናት ተያዙ።የተያዙት የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ ሀሰተኛ ሰሌዳ የለጠፉ 3 ተሽከርካሪዎች፣ የመኪና መለዋወጫዎች፣ መድኃኒቶች፣ ጥራቱ ያልተረጋገጠ የፊት ክሬም፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቅሽር ቡና፣ የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች፣ የምግብ ዘይት፣ አደንዛዥ ፅጽና ሀሺሽ፣ ሲጋራና የተለያዩ ዓይነት ብረታ ብረቶች ናቸው።የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በድሬዳዋ ላጋር ጉምሩክ፣ አዲስ አበባ ቃሊቲ ጉምሩክ፣ ጅግጅጋ፣ ሀረር፣ አዋሽ፣ ሞጆ፣ ሀዋሳ፣ ኮምቦልቻ፣ ወልዲያ፣ ባቲ እና ሌሎች ኬላ ጣቢያዎች የተያዙ ሲሆን፥ እቃዎቹም በህገ-ወጥ መንገድ ሊገቡ እና ሊወጡ ሲሉ መያዛቸውን ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።", "passage_id": "cd89bce102441bd81013f2ce478a39e7" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ህዳር 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከህዳር 11 እስከ ህዳር 17 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ከ42 ሚሊየን 749 ሺህ ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች ጥይት፣ አደንዛዥ ዕጽ፣ ቡና፣ ግመሎች እና የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች በተለያዩ የጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ተይዘዋል፡፡አልባሳት፣ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች፣ የመዋቢያ ቁሳቁሶችና መለዋወጫዎች፣ ሺሻ፣ ገቢና ወጪ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸውንም ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ዕቃዎቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ በተለያዩ የጉሙሩክ ጣቢያዎች በጉሙሩክ ሰራተኞች፣ በህብረተሰብ ጥቆማ፣ በክልል ፖሊስ፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በአድማ በታኝና በመከላከያ አባላት የጋራ ጥረት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ከኮንትሮባንድ ዕቃዎች ማስተላለፍ ጋር ተያይዞ የተለያዩ አካላትና አሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጣራ ይገኛል፡፡", "passage_id": "2e5f580c0d312bf1b130670611ed04df" }, { "passage": "ሁለት የውጭ አገር ዜግነት ያላቸው ሰዎች ከ28.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት አደንዛዥ ዕፅ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በኩል ለማሳለፍ ሲሞክሩ፣ ረቡዕ ኅዳር 24 ቀን 2012 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በጉምሩክ ኢንተለጀንስና በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ሠራተኞች የተያዙት ተጠርጣሪዎች፣ የደቡብ አፍሪካና የአዘርባይጃን ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች ናቸው ተብሏል፡፡A08864208 መለያ ቁጥር ያለው ፖስፖርት ባለቤት የሆነችው ደቡብ አፍሪካዊቷ ሞዛምቢክ ግላዲየስ ቦዛ 4.4 ኪሎ ግራም ኮኬይን ተገኝቶባታል፡፡ ከደቡብ አፍሪካ በመነሳት ወደ ህንድ ደልሂ በማጓጓዝ ላይ ሳለች፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በቁጥጥር ሥር መዋሏ ተገልጿል፡፡የአዘርባጃን ዜግነት ያላት ሁለተኛዋ ተጠርጣሪ አንቲቃ ሱማይማን ቂዚ አራት ኪሎ ግራም ኮኬይን እንደተገኘባት ታውቋል፡፡ 2722082 መለያ ቁጥር ያለው የአዘርባይጃን ፖስፖርት የያዘችው ቂዚ ረቡዕ ዕለት ጠዋት ከሞስኮ አዲስ አበባ መግባቷን፣ ሆቴል አርፋ ተመልሳ ወደ ባንኮክ ልትወጣ ስትል ከእነ ኮኬይኑ በቁጥጥር ሥር መዋሏ ሪፖርት ተደርጓል፡፡ባለፉት ሦስት ወራት አደገኛና አደንዛዥ ዕፆችን በኢትዮጵያ ሲያዘዋውሩ የተገኙ 24 የውጭ አገር ዜጎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን፣ የፌዴራል ፖሊስ ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኮሚሽኑ በመጀመርያው ሩብ ዓመት ሻሸመኔ አካባቢ ባካሄደው ዘመቻ በተሽከርካሪ ሊጓዝ የነበረ 595 ኩንታል በ135 ሔክታር መሬት ላይ የበቀለ ካናቢስ እንዲወገድ አድርጓል፡፡ በዚህ ሕገወጥ ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦች አርሶ አደሮች እህል አምርተው ከሚያገኙት የተሻለ ገንዘብ እንደሚያገኙ በመስበክ እንደሚስቧቸው ተገልጿል፡፡ በአዲስ አበባ ለልማት ታጥረው በቆዩ ቦታዎች ካናቢስ በቅሎ መገኘቱንም ባለፈው መዘገባችን አይዘነጋም፡፡ ", "passage_id": "e704a3e56875f0c8c8485efaf99bb110" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 3፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህዳር ወር ከ268 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ የገቢና የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎችና ህገ ወጥ ገንዘብ መያዝ ተችሏል፡፡ግምታዊ ዋጋቸው ብር 213,620,309 የሆኑ የገቢ ኮንትሮባንድ እቃዎችና ህገ-ወጥ ገንዘብ ግምታዊ ዋጋቸው 54,526,384 ብር ወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎችና ህገ-ወጥ ገንዘብ ከሃገር ሊወጡ ሲሉ ተይዘዋል፡፡ በአጠቃላይ በህዳር ወር 268,146,693 ብር የሚገመቱ የገቢና የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎችና ህገ ወጥ ገንዘብ መያዝ ተችሏል፡፡ በገቢ ከንትሮባንድ ከተያዙ እቃዎች ከፍተኛውን ደረጃ የያዙት ኤሌክተሮኒክስ፣ ኮንትሮባንድ ጭነውና በኮንትሮባንድ የገቡ ተሽከርካሪዎች፣ አዳዲስ አልባሳት፣ ኮንትሮባንድ ጭነው የተቀጡ ተሽከርካሪዎች እንዲሁም ምግብና መጠጥ ነክ ቁሳቁሶች ናቸው፡፡ገቢ ኮንትሮባንድ በስፋት የተያዘበት ጅግጅጋ፣ ሀዋሳ፣ ድሬደዋ፣ ሞያሌ እና አዋሽ ሲሆኑ ሌሎች ቅረንጫፍ ፅ/ቤቶችም በየደረጃው ገቢ ኮንተሮባንድን መያዝ ችለዋል፡፡ በብዛት የተያዙ ወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎች አደንዛዥ እፅ፣ የግብርና ምርቶች፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እንዲሁም ማዕድናት እና የቁም እንስሳት ናቸው፡፡በወጪ ኮንተሮባንድ ቁጥጥር ሞያሌ፣ አዋሳ፣ ባህርዳር፣ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ እና ድሬደዋ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱ ሲሆኑ፤ አሶሳ፣ ጅማ፣ ጅጅጋ እና ጋላፊ በተመሳሳይ የተሻለ የቁጥጥር ስራ ሰርተዋል፡፡በዚህ ተግባር የተሳተፉ 95 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል የተቻለ ሲሆን ተጠርጣሪዎች በጉምሩክ፣ በክልል ፖሊስ፣ በፌዴራል ፖሊስና በመከላከያ አባላት የተያዙ መሆናቸውን ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡", "passage_id": "e837b7e9cf73e51d862184288ddc07d0" } ]
53d08a3894cc5f7e43d5b88fbd5733e1
8d900c98c1599c1ee034790b209442b9
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአፋር ክልል ሕግ የማስከበር ዘመቻ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ድጋፍ አደረገ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህወሓት ጁንታ ቡድን በሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ በከፈተው ጦርነት ሳቢያ በተለያዩ አጎራባች ክልሎች በሕግ ማስከበር ሥራ ለተሳተፉ የልዩ ኃይል እና የሚሊሻ አባላት እንዲሁም የተፈናቀሉ ዜጐችን ለመደገፍ ቃል በገባው መሠረት 2ሺህ 400 ኩንታል እህል ለአፋር ክልል አስረክቧል።ድጋፉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ምክትል ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ እና የአዲስ አበባ ከተማ አቃቢ ሕግ ቢሮ ኃላፊ አብዱልቃድር መሀመድ ለአፋር ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኃላፊ ለአቶ መሀመድ ሁሴን አስረክበዋል።የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በተወካያቸው በኩል ባስተላለፉት መልዕከት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላደረገው ድጋፍም በክልሉ ሕዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጁንታው የጥፋት እኩይ ተግባር ምክንያት ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን ለመደገፍ ለአፋር ክልል 6 ሚሊዮን ብር የሚገመት የዓይነት እና 94 ሚሊዮን ብር በጥሬ ገንዘብ በጠቅላላው 100 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪ የተገኘው መረጃ ያመለክታልአዲስ ዘመን ታህሳስ 19/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38313
[ { "passage": "በኢትዮጵያ ለሚገኙ የልማት አጋሮች ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በትግራይ ክልል ህግ ለማስከበር ከተወሰደው እርምጃ በኋላ የክልሉን ሰላም ወደ ነበረበት ለመመለስ ስለተደረገው እርምጃ በገንዘብ ሚኒስትሩ በአቶ አህመድ ሺዴ እና በሰላም ሚኒስትሯ በወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ዛሬ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡አቶ አህመድ ህግ የማስከበር እርምጃው የሰላማዊ ሰዎችን ህይወት ለአደጋ በማያጋልጥ ሁኔታ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀ መሆኑን ገልጸው፣ የኢትዮጵያ መንግስት የሰብአዊ እርዳታ ጥረቱን በመደገፍ ረገድ የልማት አጋሮች ያበረከቱትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡ ሁሉም የልማት አጋሮች ኢትዮጵያ የቀጠናው የሰላም ማእከል እንድትሆን ከጎኗ እንዲቆሙም ጥሪ አቅርበዋል፡፡አያይዘውም በትግራይ ክልል ሓላፊነት በማይሰማው ወንጀለኛው ቡድን የወደሙትን የትራንስፖርት፣ የውኃ፣ የኤሌክትሪክና የቴሌኮሙዩኒኬሽን መሠረተ-ልማቶችን በመጠገን ክልሉን መልሶ በማቋቋም ወደ ነበረበት የመመለስ ጉዞ መጀመሩን አስረድተዋል፡፡የመሠረተ ልማቶቹ መውደም ምግብ እና መድኃኒት የመሳሰሉትን የሰብአዊ ድጋፎችን ለማድረስ ጊዜያዊ ድልድዮችን በአስቸኳይ መገንባት የጠየቀ በመሆኑ በሰብአዊ ድጋፉ ምላሽ ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩንም አመልክተዋል፡፡የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርም የከተማ አስተዳደሮችን በማዋቀር ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ላይ መዋቅር በመዘርጋት የተሻለ የሰብአዊ ድጋፍ ተደራሽነትና አፈጻጸም እንዲኖር ቁልፍ ሚና መጫወቱንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው፣ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸው ከተባበሩት መንግሥታት ጋር በቅንጅት የሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ ለትግራይ ክልል እና ጉዳት በደረሰባቸው አጎራባች የአማራና የዐፋር ክልሎች ሲያከናውን መቆየቱን አስረድተዋል፡፡በአንዳንድ ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት በመጀመሩ፣ በአካባቢ ላሉ ገበያዎች አስፈላጊ ሸቀጦች ተደራሽ እንዲሆኑ ጥረት በመደረጉ እና የብሔራዊ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ለ1.8 ሚሊዮን የክልሉ ህብረተሰብ የሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ ማድረግ በመቻሉ በክልሉ ሕይወት ወደ ቀድሞው ሁኔታ እየተመለሰ መሆኑን ሚኒስትሯ ገልጸዋል፡፡የልማት አጋሮች ድጋፍ ቡድን 30 ዓለም አቀፍ በይነ መንግስታት እና የመንግስታት ትብብር የልማት አጋሮችን ያቀፈ ቡድን ሲሆን፣ ዓላማውም በኢትዮጵያ የፖሊሲ ውይይት እንዲጎለብት እና የልማት አጋሮች ድጋፍ ውጤታማ እንዲሆን ማስተባበር እንዲሁም በብሔራዊ ፕላን እና ዘላቂ ልማት ግቦች ላይ የክትትል እና ግምምገማ ተግባሮችን ማከናወን መሆኑን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡", "passage_id": "1e3577e8f3a44707301ea7cdf6da3139" }, { "passage": "በ2011 አ/ም መጨረሻ እና በአዲሱ አመት መጀመሪያ ላይ የተከበሩ በአላት በሰላም ለመጠናቀቃቸው መላው የፀጥታ ሀይልና ህብረተሰቡ ላደረጉት አሰተዋፅኦ ፌዴራል ፖሊስ አመሰገነ፡፡ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ለእሬቻ በአል ስኬትም የአዲስ አበባ ህዝብና የበአሉ ተሳታፊዎች ላደረጉት አሰተዋፅኦ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡መግለጫዉን የሰጡት በፌዴራልፖሊስ የወንጀል ዘርፍ ሃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ ህዝቡ እንደሃገር የሚከበሩ በአላትና አህጉራዊና አለምአቀፋዊ ስብሰባዎች በሚኖሩበት ጊዜ ለዝግጅቶቹ ስኬቶችና በሰላም መጠናቀቅ የሚያደርገዉን አስተዋፅኦ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል፡፡ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አሳሳቢ እየሆነ የመጣዉ ህገ-ወጥ የጦር መሳርያ ዝዉዉር ችግርን ለመፍታት የሚከናወነዉ ስራ ዉጤታማ ቢሆንም የችግሩን አሳሳቢነት የሚረዳዉ ፖሊስ ህብረተሰቡ አሁንም ከጎኑ እንዲቆም ጥሪ አቅረቧል፡፡በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች እየተነሱ ባሉ ግጭቶች ሰላማዊ ሰዎችና ህግ አስከባሪዎች በስፋት ለጉዳት እየተዳረጉ መሆናቸዉንም ፖሊስ ገልጿል፡፡ህዝብና ህዝብ መቼም ቢሆን ተጋጭቶ አያዉቅም ያለዉ ፖሊስ ለራሳቸዉ ሲሉ ችግሮችን የሚፈጥሩ አካላት ከድርጊታቸዉ እንዲታቀቡ ፖሊስ ጠይቋል፡፡በያዝነዉ አመት ከሚከናወኑ ስራዎች የፌዴራል ፖሊስን ማዘመን እንደሚገኝበት የተናገሩት ሃላፊዉ በምድርና በአየር ጭምር ደረጃዉን በጠበቀ መልኩ ሰራዉን ማከናወን የሚያስችል አደረጃጀት ዕዉን ይደረጋል ብለዋል፡፡  ", "passage_id": "19afab21f40e809ffe5eda6b5d5c2163" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ለሀገሬ ሰላም ዘብ እቆማለሁ፤ ለመከላከያ ሰራዊት ቅድሚያ እሰጣለሁ በሚል መሪ ቃል 4ኛው የማሰ ስፖርት ላይ ተሳትፈዋል።", "passage_id": "fa958034dbe86d1d142397e05b675afb" }, { "passage": "የድሬዳዋ ከተማ የወንዶች ቡድን የአንድ ወር ሙሉ ደሞዛቸውን በመለገስ የተጀመረው መልካም ተግባር በሌሎች የስፖርት ተቋማትም ቀጥሏል።በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል እና አቅመ ደካሞችን ለመርዳት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ በቀጠለበት በዚህ ጊዜ የድሬዳዋ ከተማ ስፖርት ኮሚሽን በዛሬው ዕለት ግምቱ ሦስት መቶ ሺህ ብር የሚያወጣ የምግብ እህል እና ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉ ታውቋል። በተመሳሳይ የድሬዳዋ ዳኞች እና የጨዋታ ታዛቢዎች (ኮሚሽነሮች) የሙያ ማኀበር የ15 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።ከሰሞኑ የድሬዳዋ የወንዶች ቡድን ከአንድ ሚልየን ብር በላይ የሚገመት ገንዘብ የወር ደሞዛቸውን በመስጠት የጀመረው ልግስና በሴቶች ቡድኑ፣ በክለቡ የደጋፊዎች ማኀበር አማካኝነት ቀጥሎ የገንዘብ፣ የቁሳቁስ እየተደረገ ይገኛል። በከዚህ በተጨማሪ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች በድሬደዋ አካባቢዎች በመዟዟር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብሮችን እያደረጉ መሆኑን ሰምተናል።", "passage_id": "74a63d450ad3d21517b6fe7afeaa424c" }, { "passage": "በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- መንግሥት በትግራይ ክልል የሚያካ ሂደውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ:: ይህ የተገለፀው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ኬንያ እና ማላዊ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በተወያዩበት ወቅት ነው::እንደ ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ዘገባ፤ ውይይቱ ቅዳሜ ህዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም በበይነ መረብ (ቨርቹዋል) የተካሄደ ሲሆን፤ በወቅቱም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኬንያ እና ማላዊ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በዚህ ፈታኝ ጊዜ ላሳዩት ሀገራዊ ስሜት እና ላደረጉት ድጋፍ አመስግነው መንግሥት በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል የሚያካሂደውን ሁለንተናዊ ሰብዓዊ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለተሳታፊዎቹ ገልፀውላቸዋል።ሀገራችን ከውስጧ በተነሱ ከሃዲዎች ሉዓላዊነታችንን አደጋ ላይ የጣለውን፣ ጭካኔና አሳፋሪ ድርጊት የተፈፀ መበትን ሁኔታ ለመለወጥ፣ ሕግን ለማስከበር፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ መንግሥታችን ያካደሄው ፈጣንና ውጤታማ ተልዕኮ በሕዝባችን ድጋፍና አብሮነት፣ በቁርጠኛው መከላከያ ሠራዊታችን እና ልዩ ልዩ የፀጥታ አካላት አብሮ በመዋደቅ የተገኘው ድል የሁላችንም ድልና ኩራት ነው ብለዋል።በዚህ ኢ-ሰብዓዊና ጭካኔ በተሞላበት ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦች ለሕግ እንዲቀርቡም መንግሥት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንሚሠራም ተናግረዋል። በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ መንግሥትና አቋሞች በማስረዳት፣ ለመልሶ ማቋቋሙ እና ዳግም ግንባታው አስተዋጽኦ በማድረግ መንግሥት በሚያደገርው ጥረት እንዲደግፉም ጥሪ አቅርበዋል።በኬንያ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር መለስ ዓለም በበኩላቸው፣ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት አገራችን በህወሓት አፍራሽ ሃይል ተገዳ ወደ ሕግ ማስከበር መግባቷን ተከትሎ በኬንያ እና ማላዊ የሚኖሩ ወገኖቻችን ላሳዩት የጋለ ብሔራዊ ስሜት እና ላደረጉት ድጋፍ አመስግነዋል። መንግሥት እያካሄደ ያለውን የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን የመጠበቅ እና የዜጐችን ደህንነት የማስከበር ዘመቻ እንዲሳካ በኬንያና ማላዊ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሙያተኞች እና ነጋዴዎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ጠቅሰው፤ በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸው ባላቸው ግንኙነት የህዝብ አምባሳደር ሆነው ስለአገራቸው አቋምና ፍላጐት ዘብ መቆማቸውን ተናግረዋል። በቀጣይም ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ፣ የተፈናቀሉትን ለማቋቋም እና የፈረሰውን ለመገንባት መንግሥት በሚያደርገው ዲያስፖራው የሚጠበቅበትን ሁሉ እንደሚያደርግ ሚሲዮኑ ሙሉ እምነት እንዳለውም አምባሳደር መለስ ገልፀዋል::አዲስ ዘመን ታህሳስ 5/2013", "passage_id": "aa80217851fe4a53a40a157545a7b2a6" } ]
bc5048760f511d51e74e717001d4c21d
0144ad88e4be9c873dc8c3c50637e0f6
ለኦሎምፒክ የተመረጡ አትሌቶች ከመጪው ሳምንት ጀምሮ ወደ ዝግጅት ይገባሉ
ዓለምን እያሳሰበ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሳቢያ መካሄድ አለመካሄዱ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አምስት ወራት የቀሩት ቢሆንም በርካታ የዓለማችን አገራት በተለያዩ ስፖርቶች የሚያደርጉትን ዝግጅት አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ኢትዮጵያም በዚህ ታላቅ የስፖርት መድረክ በተለይም በአትሌቲክስ ረጅምና መካከለኛ ርቀቶች ውጤታማ እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በቀድሞው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አባዱላ ገመዳ የሚመራ ብሔራዊ የዝግጅት ኮሚቴ በማዋቀር የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ሰንብቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውጤት በሚጠበቅበት የአትሌቲክስ ስፖርት ኢትዮጵያን እንዲወክሉ የተመረጡ አትሌቶች ከመጋቢት ሦስት ጀምሮ ወደ ሆቴል ገብተው ዝግጅት እንዲጀምሩ ውሳኔ ላይ መድረሱን ያሳወቀ ሲሆን፣ አትሌቶችና አሰልጣኞች ከትናንት ጀምሮ በኦሊምፒክ ኮሚቴ ፅሕፈት ቤት በአካል በመገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሁለት ሳምንት በፊት በኦሊምፒኩ ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችና አሰልጣኞችን መልምሎ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በመካከለኛ ርቀት፣ ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል፣ ረጅም ርቀት፣ ማራቶንና ርምጃ ውድድሮች አሰልጣኞችና አትሌቶች መመረጣቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት በመካከለኛ ርቀት አሰልጣኝ ብርሃኑ መኮንን፣ ሃብታሙ ግርማ፣ ኢሳ ሽቦ እና ጉዲሳ ታሱ በአሰልጣኝነት ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም ኃይለማሪያም እና ስንታየሁ ካሳሁን ደግሞ በተጠባባቂነት ተይዘዋል፡፡ በ3ሺ ሜትር መሰናክል ደግሞ አሰልጣኝ ተሾመ ከበደ እና ዶክተር ብዙአየሁ ታረቀኝ ሲመረጡ አሰልጣን ከፍያለው አለሙ ተጠባባቂ ሆነዋል፡፡ አገሪቷ በኦሊምፒክ መድረክ በተለይ ውጤታማ በሆነችባቸው የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር ርቀቶችም አራት አሰልጣኞች ተመራጭ ሆነዋል፡፡ አሰልጣኝ ሁሴን ሸቦ፣ ቶሌራ ዲንቃ፣ ንጋቱ ወርቁ እና ኃይሌ እያሱ ሲመረጡ፤ አሰልጣኝ ተፈሪ መኮንን እና በሪሁን ተስፋይ ደግሞ የተጠባባቂነት ስፍራን ይዘዋል፡፡ በረጅሙ የአትሌቲክስ ውድድር ማራቶን በማናጀር አሰልጣኝነት ስኬታማ የሆኑት አሰልጣኝ ሃጂ አደሎ ከሌላው ስኬታማ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ጋር በመሆን የርቀቱን እንዲመሩም ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኝ ጌታነህ ተሰማ እና ይረፉ ብርሃኑ ደግሞ ተጠባባቂ ሆነው ተይዘዋል፡፡ የእርምጃ ቡድኑም በሻለቃ ባየ አሰፋ አሰልጣኝነት የሚያመራ ይሆናል፡፡ ውጤት በሚጠበቅበትና ታሪካዊ ሊሆን እንደሚችል በሚታሰበው የወንዶች ማራቶን ውድድር የ5ና 10ሺ ሜትር የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑና የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ባለፈው መስከረም በበርሊን ማራቶን ባስመዘገበው ፈጣን ሰዓት መሰረት በዋናነት መመረጡ የሚታወስ ሲሆን ማራቶንን ጨምሮ በሌሎች ርቀትም ጠንካራ አትሌቶች በቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን ለመወከል ወደ ዝግጅት ይገባሉ፡፡ ከነዚህም መካከል በዶሃው ቻምፒዮና ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው አትሌት ሞስነት ገረመው 2፡02፡55 የሆነ ሰዓት ባለፈው ለንደን ማራቶን ላይ በማስመዝገቡ በማራቶን ቡድኑ ውስጥ በሦስተኛ ደረጃ ተመራጭ ሆኗል፡፡ ብርሃኑ ለገሰ በ2፡02፡48 በሁለተኛነት ሲመረጥ የዓለም ሻምፒዮኑ አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ ከሌሎች አትሌቶች አኳያ ያለው የቅርብ ጊዜ ፈጣን ሰዓት በቡድኑ ሊያካትተው እንደማይችል ይፋ ከተደረገው የእጩዎቹ ዝርዝር መረዳት ተችሏል፡፡ በሴቶች ማራቶን የዱባይ ማራቶን አሸናፊዋ ወርቅነሽ ደገፋ 2፡17፡41 ሰዓት በመያዝ በቀዳሚነት ስሟ ሲቀመጥ ሮዛ ደረጄ 2፡18፡30ና በ2፡18፡34 ሰዓት ሩቲ አጋ በቀዳሚነት ታጭተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በሚጠበቁበት የአስር ሺ ሜትር ውድድር የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ አሸናፊው ዮሚፍ ቀጄልቻ 26፡49፡34 በሆነ ሰዓት ሲመረጥ አንዱአምላክ በልሁ 26፡53፡15ና በ26፡54፡34 ጀማል ይመር በቀዳሚነት ተመርጠዋል፡፡ በሴቶች የኦሊምፒክ ቻምፒዮኗ አልማዝ አያና ከዓመት በላይ በጉዳት ላይ የቆየች ቢሆንም ቀዳሚዋ ተመራጭ መሆን ችላለች፡፡የዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ባለቤቷ ለተሰንበት ግደይና ነፃነት ጉደታም ከቀዳሚዎቹ እጩዎች መካከል ተካተዋል፡፡ በወንዶች አምስት ሺ ሜትር በዶሃው የዓለም ሻምፒዮና የወርቅና የብር ሜዳሊያ ያጠለቁት ሙክታር ኢድሪስና ሰለሞን ባረጋ እንዲሁም ሃጎስ ገብረህይወትና ጥላሁን ሃይሌ በቀዳሚነት ሊመረጡ ችለዋል፡፡ በሴቶች ደግሞ ጸሐይ ገመቹ፣ ሐዊ ፈይሳና ፋንቱ ወርቁ ባስመዘገቡት ሰዓት መሰረት ሊመረጡ ችለዋል፡፡ኢትዮጵያ በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ከአትሌቲክስ ውድድሮች በተጨማሪ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ተሳታፊ መሆኗን ከሁለት ሳምንት በፊት ማረጋገጥ ችላለች፡፡ በሞሮኮ ራባት ተካሂዶ በነበረው የወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት የኦሊምፒክ ማጣሪያ ውድድር ማስተር ሰለሞን ቱፋ በኦሎምፒክ እንደሚወዳደር ማረጋገጡ አይዘነጋም፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 28/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28667
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝግጅትን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሄደ።በመድረኩ ላይ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝግጅትን አስመልክቶ የመነሻ ሰነድ፣ ለቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ስለ ስፖርት ህክምና እና የፀረ አበረታች ቅመሞች ቁጥጥርና ክትትል ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።ከመድረኩ ተሳታፊዎችም የተለያየ ሃሳብና አስተያየት ቀርቦ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጂሎ፥ ውድድሩ ከቀረው ጊዜ አንጻር ለዝግጅቱ መሳካት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።የምክክር መድረኩ የአቋም መግለጫ በማውጣት መጠናቀቁን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።", "passage_id": "ea9373d3fcf5787ca874e600973cb440" }, { "passage": "\nአለምአቀፉ የኦሎምፒክ ኮሚቴ ከትናንት ጀምሮ እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ስብሰባ የቶኪዮ 2020 የኦሎምፒክ ውድድርን ለሌላ ጊዜ ማስተላለፍን ጨምሮ ሌሎች አማራጮችን እያየ ይገኛል፡፡\nኮሚቴው የተሰበሰበው እየተስፋፋ የመጣው ኮሮና ቫይረስ በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ላይ ጥላ መጣሉን ተከትሎ ነው፡፡ ኮሚቴው ኮሮና ቫይረስ ሁለት አማራጮችን እንዲያስቀምጥ እንዳስገደደው አስታውቋል፡፡\nኦሎምፒኩ የሚጀመርበትን ሐምሌ 17ን ወደ ኋላ መጎተት ወይንም ወድድሩን በአንድ አመት ወይንም ከዚያ በላይ ወደፊት መግፋት ሲሆን መሰረዝ ግን ችግሩን እንደማይፈታና ማንንም እንደማይጠቅም ኮሚቴው አስታውቋል፡፡ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ “ስለዚህ መሰረዝ አጀንዳ አይደለም”፤ ዝርዝር ውይይቶች በሚቀጥሉት አራት ሳምንታት ይካሄዳሉ ብሏል፡፡\nየኮሚቴው ኦሎምፒኩን ለማስተላለፍ ማሰቡ በአለም አትሌቲክስ፣በአለምአቀፍ ፓራኦሎምፒክ ኮሚቴና በትላልቆቹ ብሄራዊ የኦሎምፒክ ኮሚቴዎች በበጎ ተወስዷል፡፡\nኮሚቴው በከፊልም ቢሆን ሀሳቡን ለመቀየር የወሰነው፣ ከአትሌቶች፣ከፌደሬሽኖችና ከብሄራዊ ኮሚቴዎች የመጣውን ጫና ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የቶኪዮ ኦሎምፒክ አዘጋጆች ግን ወድድሩ በተያዘለት ጊዜ እንዲካሄድ እየወተወቱ ይገኛሉ፡፡\n\n\n", "passage_id": "dd9ba197cb508034d684b1fe8606cd94" }, { "passage": "ኢትዮጵያ\nዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በሀገር አቋራጭ ውድድር ባስመዘገቡት ስኬት በቀዳሚነት ከሚዘረዝራቸው ሀገራት መካከል ትገኛለች። በተለይ በዚህ ርቀት በሚካሄደው ዓመታዊ ሻምፒዮና ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በርካታ ሜዳሊያዎችን ሰብስበዋል። በተያዘው ሳምንት በሚካሄደው 43ኛው ሻምፒዮናም እንደ ቀድሞው ሁሉ ውጤት እንደሚመዘገብ ይጠ በቃል። የሻምፒዮናው ዝግጅት የዘንድሮ ተረኛ ሀገር ዴንማርክ ስትሆን፤ አርሁስ በተባለው ከተማ በመጪው ቅዳሜ ይጀመራል። በዚህ ተሳታፊ ለመሆን በዝግጅት ላይ የቆየው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንም ዛሬ ምሽት በአራራት ሆቴል ሽኝት እንደሚደረግለት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በዚህ ውድድር ተካፋይ የሚሆኑት አትሌቶች በቅርቡ ከተካሄደው 36ኛው የጃንሜዳ አገር አቋራጭ ውድድር ተሳትፎ ባላቸው የተሻለ ውጤት እንዲሁም የእድሜ ተገቢነትን ያሟሉ ተመርጠዋል። የተመራጭ አትሌቶች ልምድ ያላቸው አሰልጣኞችም ብሄራዊ ቡድኑን እንዲያሰለጥኑ መደረጉን ከፌዴሬሽኑ ይፋዊ ድረገጽ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል። አትሌቶቹ\nካምፕ ገብተውም ለውድድሩ የሚረዳቸውን ልምምድም በአዲስ አበባ ስታዲየም፣ በጃንሜዳ እና ከከተማ ውጪ ልዩ ልዩ ልምምዶችን ሲሰሩ ቆይተዋል። ከስፖርታዊ ስልጠናው ባሻገርም በስነ ልቦና፣ በአመጋገብ፣ በእረፍት አጠቃቀም፣ በህክምና፣ በማሳጅና ፊዚዮቴራፒ እንዲሁም በእርስ በርስ መስተጋብር ረገድ በቡድኑ አሰልጣኞች፣ አመራሮችና የህክምናው ዘርፍ ከፍ ያለ ድጋፍና ክትትል የተደረገለትም ነበር። በዚህ\nውድድር ላይ ኢትዮጵያ በጥቅሉ 28 አትሌቶችን የምታሳትፍ ሲሆን፤ 14ቱ ሴቶች 14ቱ ደግሞ ወንዶች ናቸው። ውድድሩ በአምስት ክፍሎች የሚካሄድ ሲሆን፤ ከ20ዓመት በታች 6ኪሎ ሜትር የሴቶች ውድድር፤ ዳግማዊት ገብረእግዚአብሄር፣ አለሚቱ ታሪኩ፣ ጽጌ ገብረሰላማ፣ መሰሉ በርኸ፣ ውዴ ከፋለ እና ሚዛን ዓለም ተሳታ ፊዎች ይሆናሉ። በወንዶች ከ20ዓመት በታች የወንዶች ውድድር ደግሞ፤ ጸጋዬ ኪዳኑ፣ ሚልኬሳ መንገሻ፣ ታደሰ ወርቁ፣ ጌትነት የትዋለ፣ ገብረጊዮርጊስ ተክላይ እና ድንቃለም አየለ ተሰልፈዋል። በአዋቂ ሴቶች 10ኪሎ ሜትር፤ ደራ ዲዳ፣ ለተሰንበት ግደይ፣ ዘነቡ ፍቃዱ፣ ሃዊ ፈይሳ፣ ጸሃይ ገመቹ እና ፎቶን ተስፋይ ተካፋዮች ይሆናሉ። በአዋቂ\nወንዶች የ10ኪሎ ሜትር ቡድን ደግሞ፤ ሞገስ ጥኡማይ፣ ሰለሞን ባረጋ፣ አንዷምላክ በልሁ፣ እንየው መኮንን፣ ቦንሳ ዲዳ እና አብዲ ፉፋ ተካትተዋል። ሴት እና ወንድ አትሌቶች በጋራ በሚሳተፉበት የድብልቅ ሪሌ 8 ኪሎ ሜትር ውድድርም፤ ፋንቱ ወርቁ፣ ቦኔ ጩሉቃ፣ ታደሰ ለሚ እንዲሁም ከበደ እንዳለ የሚሮጡ ይሆናል። አባጣ ጎባጣ በሚበዛበትና ፈታኝ በሆነው በዚህ ውድድር ላይ ተካፋይ የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ልምዳቸውን ተጠቅመው እንደተ ለመደው ስኬታቸውን እንደሚያበስሩም ይጠበቃል። በተለይ በረጅም ርቀት እንዲሁም በሀገር አቋራጭ ውድድሮች ብቃቱን በማስመስከር ላይ የሚገኘው ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ አሸናፊ እንደሚሆን ከወዲሁ እየተጠበቀ ነው። ሰለሞን በጃንሜዳው ሻምፒዮና ላይ በ10 ኪሎ ሜትር ሁለተኛ ቢወጣም፤ ርቀቱን የሸፈነው 31ደቂቃ ከ18ደቂቃ ከ36ሰከንድ በመግባት ነበር። ያለፈው ዓመት በስፔን በተካሄደ ሌላ ውድድር ላይም በተመሳሳይ አትሌቱ አሸናፊ መሆኑ የሚታወስ ነው። አትሌቱ\nከዚህ ባሻገር በጣሊያን በሚካሄደው ዓመታዊ የሀገር አቋራጭ ውድድር ላይ በመሳተፍ የሀገሩን ልጅ ሃጎስ ገብረህይወትን ተከትሎ በመግባት ነበር ውድድሩን ያጠና ቀቀው። በሚያሸልመው የቡድን ተሳትፎም ኢትዮጵ ያዊያን አትሌቶች በተለይ የበላይነቱን የተላበሱ ሲሆን፤ በዚህ ውድድር ላይም አሸናፊ በመሆን ተጨማሪ ሜዳሊያዎችን እንደሚያስመዘግቡ ይጠበቃል። በዚህ የው ድድር መድረክ በተለይ ባስመዘገባቸው ሜዳሊያዎች ብዛት እስካሁንም አቻ ያልተ ገኘለት ቀነኒሳ በቀለ ለአምስት ጊዜያት በተከታታይ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ሆኗል።\n\n ከ10ኪሎ ሜትር በተጓዳኝንም በ12ኪሎ ሜትር ለስድስት ጊዜያት ሻምፒዮን በመሆን ወርቃማ ታሪኩን አስመዝግቧል። ቀነኒሳ በዚህ ውድድር አጭር ርቀትም ስኬታማ ሲሆን፤ አምስት የወርቅና አንድ የብር ሜዳሊያዎችን የግሉ በማድረግም ባለ ክብረወሰን ነው። እአአ በ2004 በብራሰልስ በተካሄደው ሻምፒዮና ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለ፣ ገብረእግዚአብር ገብረማሪያም እና ስለሺ ስህን በሰከንዶች ልዩነት ተቀዳድመው ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ የወሰዱበት ውድድር እስካሁንም እጅግ ስኬታማው ነው።አዲስ\nዘመን መጋቢት 16/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "1ca820ac1b7504490e45c57f6d6519c9" }, { "passage": "የዓለም\nትልቁ ውድድር በየአራት ዓመቱ ከሚያካሂደው ኦሊምፒክ ባሻገር፤ ተጨማሪ ውድድሮችንም እንደሚያካሂድ ይታወቃል። የፓራሊምፒክ፣ የወጣቶች፣ «ስፔሻል» ኦሊምፒክ፣… ይጠቀሳሉ። በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከዛሬ ጀምሮ የሚካሄደውም በኢትዮጵያ ብዙም ዕውቅና የሌለው የስፔሻል ኦሊምፒክ ነው። ይህ ኦሊምፒክ የአዕምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ስፖርተኞች የሚያሳትፍ ሲሆን፤ ኢትዮጵያም ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳታፊ እንደምትሆን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በድረ ገጹ አስታውቋል። በዓለም ላይ ከ200 ሚሊዮን ህዝብ በላይ የአዕምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ቢኖሩም፤ በተለይ በታዳጊ ሃገሮች የተገለሉና ለከፋ ኑሮ ተጋላጭ የሆኑ ናቸው። በዚህም ምክንየት የተለያዩ ዕድሎችን እንደማያገኙ ይታወቃል፤ በዚህም በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ለማሳተፍ በሚል ኦሊምፒኩ መካሄድ ጀምሯል። እአአ በ1968 በጆን ኦፍ ኬነዲ ቤተሰቦች በአሜሪካ ሲመሰረት፤ የመጀመሪያው ውድድርም በቺካጎ ነው የተካሄደው፡፡ ላለፉት 50 ዓመታት ውድድር በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ እአአ ከ2003 ጀምሮ ከአሜሪካ ባሻገር ሌሎች ሃገራትም እየተፈራረቁ ያስተናግዱታል። ዛሬ የሚጀመረውን ውድድርም አውስትራሊያ፣ ጀርመን እና ደቡብ አፍሪካን ያሸነፈችው የዩናይትድ አረብ ኤሜሬትሷ አቡ ዳቢ ታስተናግደዋለች። በውድድሩ ላይ ከ190 ሃገራት የተወጣጡ 7 ሺ 500 አትሌቶች በ24 ስፖርቶች የሚፎካከሩ ይሆናል። ለውድድሩ\nዘጠኝ ስታዲየሞች የተዘጋጁ ሲሆን፤ የዛሬው የመክፈቻ ስነ-ስርዓትም በዛይድ ስፖርት ሲቲ ስታዲየም ይካሄዳል። የዛሬ ሳምንት የሚደረገው የመዝጊያ መርሐ ግብርም በዚሁ ስታዲየም ሲካሄድ፤ ባንዲራውም እአአ የ2021 ተረኛ አዘጋጅ ሃገር የሆነችው ስዊድን ትረከባለች። ለመጀመሪያ ጊዜ በመካከለኛዋ ምሥራቅ አገር የሚደረገው ውድድር ላይ፤ ከአትሌቶች ባሻገር 2 ሺ 500 አሰልጣኞችና የቡድን ልዑክ፣ ከ4ሺ በላይ የክብር እንግዶች ይገኛሉ። ከክብር\nእንግዶቹ መካከልም ዲዲየር ድሮግባ እና ሮማሪዮን የመሳሰሉ የእግር ኳስ ከዋክብቶች እንደሚገኙ ይጠበቃል። ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚሆን ህዝብ ደግሞ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ይከታተሉታል። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሳተፍ ሲሆን፤ በሁለት ወንድና ሁለት ሴት በድምሩ በአራት አትሌቶች ትወከላለች። በወንዶች በኩል አትሌት ብሩክ ፈለቀ እና አትሌት ሚሊዮን ያደታ፤ በሴቶች ደግሞ አትሌት ትግስት ኡጋሳ እና አትሌት መዓዛ ኤልያስ በውድድሩ እንደሚሳተፉም መረጃው ይጠቁማል። በውድድሩ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍ ሪካ 14 ሃገሮች ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሳተፉ ይሆናል። ይህ ስፖርታዊ ኩነትም ከስፖርታዊ ውድድር ባሻገር አካታች ማህበረሰብን ለመፍ ጠር የሚደረግ እንቅስቃሴም ነው።አዲስ\nዘመን መጋቢት 5/2011በብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "6ebe3c162dea369642e792a781dc9608" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ታህሳስ 6፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአዲስ አበባ ስታዲየም በነገው ዕለት ይጀመራል፡፡የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአጭር፣ በመካከለኛ ርቀት፣ በ3 ሺህ ሜ.መሰናክል፣ በእርምጃና በሜዳ ተግባራት ከታህሳስ 7 እስከ 12 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበበ ስታዲየም ነው የሚካሄደው፡፡በመክፈቻው እለትም የአሎሎ ውርወራ ማጣሪያና ፍፃሜ፣ የስሉስ ዝላይ ማጣሪያና ፍፃሜ፣ እንዲሁም ከ100 ሜትር እስከ 800 ሜትር የማጣሪያ ውድድሮች እንደሚካሄዱ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡", "passage_id": "a58b9627f26cfd71c2a0782674859818" } ]
a8e4023ae18f8665b3e9ef434b721864
9329df34b8dfebb71bab8b039b0495cc
«ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ» የጎዳና ላይ ሩጫ ይካሄዳል
«ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ» በሚል መሪ ቃል የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ም ለማካሄድ ፍቃድ መገኘቱን አዘጋጁ ፍቅር ያሸንፋል በጎ አድራጎት ማኅበር አስታወቀ። የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅና መስራች አቶ ሚስባህ ከድር እንደገለፁት፤ ስፖርት ጉልህ ሚናውን ከሚጫወትባቸው መስኮች አንዱ በሰላም ላይ ተጽዕኖ የመፍጠር አቅሙ ነው። ማህበሩ ይሄንኑ መሰረት በማድረግ «ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ» በሚል መሪ ቃል መስቀል አደባባይ ባዘጋጀው ውድድር ላይ 40 ሺ ተሳታፊዎች የሚጠበቁ ይሆናል።የጎዳና ሩጫው ቀደም ሲል የካቲት 15 ቀን 2012 ዓ.ም ለማካሄድ ታስቦ እንደነበር የገለፁት አቶ ሚስባህ፣ በወቅቱ በከተማው ላይ ሊከናወኑ የነበሩ የተለያዩ መርሐ ግብሮች ከመኖራቸው ጋር ተያይዞ ውድድሩን በተያዘለት ጊዜ ለማድረግ እንዳልተቻለ ተናግረዋል። አሁን ግን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽፈት ቤት ውድድሩን ለማድረግ በደብዳቤ ጥያቄ በማቅረብ ፍቃድ ማግኘት መቻሉን አብራርተዋል ለውድድሩ የሰላም ሚኒስቴር ዕውቅና የሰጠው ሲሆን አመስት ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን ውድድር ለማካሄድ ዝግጅቱ ተጠናቋል። «በዓይነቱና በይዘቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚካሄደው የጎዳና ላይ ሩጫ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ አክቲቪስቶችና ታዋቂ ግለሰቦችን፣ አርቲስቶች እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎች ያለምንም የፆታና የዕድሜ ልዩነት ይታደሙበታል›› ያሉት አቶ ሚስባህ፣ ከሩጫው መርሐ ግብር በኋላ ትልቅ እንጀራ በማዘጋጀት በአንድ ላይ የመቁረስ ሥነ ሥርዓት እንደሚኖር አስረድተዋል ይህም ‹ሰፊ እንጀራ አለን ተካፍለን እንብላ፤ እርስ በርስ አንባላ› የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ታስቦ እንደሚከናወን አክለዋል። በሽብር ወንጀል ክስ ከአራት ዓመት በላይ በወህኒ ቤት መቆየታቸውን የሚናገሩት አቶ ሚስባህ፣ የማህበሩ የክብር አምባሳደር አርቲስት ቻቺ ታደሰ እና አርቲስት ዳዊት ፅጌን በማድረግ ባለፉት 12 ወራት የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን አስታውሰዋል። የፕሮግራሙ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ የመጣውን ሰላም በጋራ በመጠበቅ የተሻለችውን ኢትዮጵያን ለትውልድ ማውረስ ይቻል ዘንድ የጋራ ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሆነም አመልክተዋል። አዲስ ዘመን መጋቢት 1/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28836
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2013 (ኤፍቢሲ)በነገው ዕለት የታላቁ የሩጫ ውድድር የሚካሄድባቸው መንገዶች ለትራፊክ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አመራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሚሽን ጠይቋል፡፡ፖሊስ የሚያደርገውን  የፀጥታ ዝግጅት በቀና መንፈስ በመተባበር የሚታወቀው መላው የመዲናዋ ነዋሪ እና የውድድሩ ተሳታፊዎች ለፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ሁሉ ትብብር እንዲያደርጉ ኮሚሽኑ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡በዕለቱ መነሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ የሚጀመረው ወድድር በአዲስ አበባ ስታዲዮም ሜክሲኮ አደባባይ በልደታ ቤተክርስቲያን በማድረግ በዛጉዌ ህንፃ በመታጠፍ-በጌጃ ሰፈር ጎማ ቁጠባ በፍልውሃ በመድረግ በካዛንቺስ በኡራኤል ቤተክርስቲያን የአትላስ መንገድ በመያዝ አክሱም ህንፃ አጠገብ መድረሻውን እንደሚያደርግ ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡በመሆኑም የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይኖር-ኮቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበልህንፃ-ከጎተራ ማሳለጫ ወደ መስቀል የሚወስደው መንገድ የቀድሞ አራተኛ ክፍልጦር-ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው ኬኬ ህንፃ ወይም ጨርቆስ ማዞሪያ-ከሳር ቤት ወደሜክሲኮ ለሚመጡ አፍሪካ ህብረት አደባባይ-ከካርል አደባባይ ወደከፍተኛ ፍ/ቤትየሚወስደውመንገድ ልደታ ፀበል-ከጦርኃይሎች ወደ ሚክሲኮ ለሚመጡ ኮካ መገንጠያ  ሜክሲኮ ለሚመጡ ጆስሐንሰን– ከመርካቶ በጎማ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ለሚመጡ በርበሬበረንዳከተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በጎማ ቁጠባ የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር (ሼልድሬንስ)-ከቸርቸር ወደ አምባሳደር ፣ ሜክሲኮ እና ለገሃር ለሚመጡ ቴድሮስአደባባይ-ከአዋሬ ወደ ካዛንቺስ ለሚመጡ ሴቶች አደባባይ-  ከመገናኛ ወደ 22 ለሚመጡ ዘሪሁን ህንፃ-ከቦሌ መድኃኒያለም የሚመጡ አትላስ ሆቴል አካባቢለተሽከርካሪ ዝግ ሲሆኑ በተጨማሪም ከውስጥ ለውስጥ መንገዶች ተወዳዳሪዎቹ ወደሚያልፉባቸው መንገዶች መውጣት በጥብቅ የተከለከለ በመሆኑ አሽከርካሪዎች ተገንዝበው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙና ለፀጥታ አካላት ተባባሪ እንዲሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ በተጨማሪም ወድድሩ በሚካሄድባቸው መንገዶች ከማለዳው 11 ሰዓት ከ 30  ጀምሮ ተሸከርካሪን ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥም ሆነ ለፖሊስ መረጃ ለመስጠት 011-1-11-01 11እና በ991 ነፃ የስልክ ቁጥሮች መጠቀም እንደሚቻል ኮሚሽን ያሳውቃል፡፡ ", "passage_id": "9a71d66ca460b0e3e92154729ba90a5b" }, { "passage": "ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ህዳር ላይ ለሚካሄደው የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ከተለዩ ቦታዎች የሚመጡ አትሌቶችን መዝግቦ ከተመዘገቡት ውስጥ በእጣ ለይቶ ውድድሩ ላይ ሲያሳትፍ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በዚህ ዓመት ግን የሚቀጥለውን ምርጥ አትሌት ለማውጣት ለመጀመሪያ ጊዜ ለአትሌቶቹ ከታላቁ ሩጫ በፊት የሚካሄድ የማጣሪያ ውድድር አዘጋጅቷል፡፡ የአትሌቶች ማጣሪያ ውድድርም ነገ በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ከጠዋቱ 1፡00 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ በታንዛኒያ አስተናጋጅነት በህዳር ወር ይደረጋል። አዘጋጆቹም የምድብ ድልድሉን ይፋ አድርገዋል። በዚህም መሰረት በምድብ ‹‹ሀ›› ታንዛኒያ፣ ብሩንዲ፣ ዛንዚባር እና ደቡብ ሱዳን ተደልድለዋል፡፡ በምድብ ‹‹ለ›› ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ኢትዮጵያና ጅቡቲ ይገናኛሉ:: ውድድሩ ከኅዳር 4-13 ድረስ በቻማዚ ስታዲየም የሚደረግ ሲሆን ዓርብ ኅዳር 5 ቀን 2012 ዓም ኢትዮጵያ የመጀሪያውን ጨዋታ ከኬንያ ጋር ታደርጋለች፡፡ የኢትዮጵያ ሴት ብሔራዊ ቡድን ከበጀት ጋር ተያይዞ ወደ ውድድሩ ሊያቀና እንደማይችል እየተገለፀ ቢሆንም ሉሲዎቹ የአንድ ሳምንት ዝግጅት አድርገው ወደ ታንዛኒያ ሊያቀኑ እንደሚችሉ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡የቤሩት ማራቶን ተራዘመ በዓለም አትሌቲክስ የብር ደረጃ የተሰጠው የቤሩት ማራቶን በአገሪቱ ያለውን ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ተከትሎ መራዘሙ ታውቋል:: ባለፉት አስራ ስድስት ዓመታት ሲካሄድ የቆየው ይህ ውድድር የአገሪቱን ዜጎችና ሌሎች የዓለማችን አትሌቶችን በማነቃቃትና የውድድር እድል በመፍጠር ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ ለውድድሩ አሸናፊዎች መቶ ሃምሳ ሺ ዶላር በመክፈልም በዓለማችን ውድ ከሆኑ የጎዳና ላይ ውድድሮች አንዱ መሆን ችሏል፡፡ የውድድሩ ፕሬዚዳንት ሜይ ኤልካሊ ትናንት እንደገለፁት ውድድሩ የሚካሄድበት ቀን በውል ባይታወቅም አዘጋጆቹ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለማካሄድ እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ ሲቲ ካፑ ጦሩን ከፈረሰኞቹ\nአገናኝቷል የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የምድብ ድልድል ከትናንት በስቲያ ይፋ ተደርጓል:: በ8 ክለቦች መካከል የዕጣ አወጣጡ ሥነሥርዓት ተካሂዶ በምድብ «ሀ»ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ባህር ዳር ከተማ ፣ወልቂጤ ከተማና መከላከያ ተደልድለዋል። በምድብ «ለ» ደግሞ ኢትዮጵያ ቡና ፣ኢትዮ ኤሌክትሪክ ፣ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ሰበታ ከተማ ተደልድለዋል። በመክፈቻ ጨዋታ ጥቅምት 22 ቀን ከምድብ ‹‹ሀ›› ባህርዳር ከነማ ከወልቂጤ ከነማ በ8 ሰዓት ፣ ቅዱስጊዮርጊስ ከመከላከያ በ10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚገናኙ ታውቋል፡፡ ጥቅምት 24 ቀን ኢትዮጵያ ቡና ከሰበታ ከነማ ፣ ኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሏል።አዲስ\nዘመን\nጥቅምት 15/2012", "passage_id": "6667ecefe66dc283b5f8738747cb5051" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ፣ አዲስ አበባ ላይ ውበት ለመጨመር የወጠኑ ወጣቶች እንቅስቃሴ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ለወትሮው በማስታወቂያ ወረቀቶች ውበታቸውን አጥተው የነበሩ የመንገድ ዳር ግንብ እና ግድግዳዎችን በውብ የስዕል ስራዎች አስጊጠዋል፣ ተስፋቸውን እና ህልማቸውን ለተመልካች አቅርበዋል፥አሁን ላይ ደግሞ ከደጋፊ ተቋማት ጋር በተባበር ወጣቶቹ -የጎዳና ላይ ስዕሎችን በመጠቀም የተለያዩ ማህበራዊ መልዕክቶችን በአዲስ መልክ እያስተላለፉ ነው። የቡድናቸው ስም አዲስ የጎዳና (አደባባይ) ጥበብ ይሰኛል። የቡድኑ አጋር መስራች ሰለሞን ክፍሌ የቡድኑን አጀማመር እና ህልም አጋርቶናል።\n", "passage_id": "1fe7daf505793a317c15ae91e410d5bb" }, { "passage": "የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሰባት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰዎች ይሳተፋሉ።የግድቡ ግንባታ የተጀመረበትን ሰባተኛ ዓመት አስመልክቶ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ሩጫ “ስለ ዓባይ እሮጣለሁ” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ሲሆን ሩጫውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን፣ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በጋራ አዘጋጅተውታል።የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሩጫ አቢይ ኮሚቴ አባልና የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ዳርጌ እንደገለጹት፤ ከ100 በላይ በሚሆኑ ከተሞች በሚከናወነው ሩጫ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይሳተፋል።ለሩጫው 250 ሺህ ካናቴራ ለሽያጭ የተዘጋጀ ሲሆን ከሽያጩ 25 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቅሰዋል።ከተሳታፊው ቁጥር አንጻር ያለው የሩጫ ካናቴራ በቂ ባለመሆኑ መግዛት ያልቻሉ የህብረተሰብ ክፍሎችም በሩጫው መሳተፍ እንደሚችሉ ተናግረዋል።ሩጫው በሁሉም ቦታዎች ከንጋቱ 12 ሰአት ከ30 ደቂቃ እንደሚጀመር የገለጹት አቶ ዳንኤል በዚህ ሩጫ ላይ 90 ሺህ የሚሆኑ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም እንደሚሳተፉ ገልጸዋል።በአዲስ አበባ የሚካሄደው ውድድር መነሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ፣ በሜክሲኮ ቡናና ሻይ፣ በገነት ሆቴል ቄራ – ቄራ መገንጠያ በጎተራ ማሳላጫ አድርጎ መድረሻው መስቀል አደባባይ እንደሆነ ታውቋል።በመዲናዋ በሚካሄደው ውድድር የድንገተኛ አደጋ የህክምና ባለሙያዎች መኖራቸውንና ለህክምና እርዳታ አምቡላንሶች እንደተዘጋጁም አመልክተዋል።ሩጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ከጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንደተካሄደም አንስተዋል።ከገቢ ማሰባሰብ ባሻገር ሩጫው ህብረተሰቡ ስለ ህዳሴው ግድብ ንቅናቄ መፍጠርና ግድቡ የቀን ተቀን አጀንዳ አድርጎ እንዲንቀሳቀስ አላማ ያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።ከዚህ በፊት በ2005 እና በ2009 ዓ.ም በተካሄዱ ተመሳሳይ ሁለት ውድድሮች በአጠቃላይ ከ760 ሺህ በላይ ሰዎች መሳተፋቸውን አውስተዋል።የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሩጫ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኝና እንዲመዘገብ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አቶ ዳንኤል ጠቁመዋል።በአዲስ አበባው ውድድር በሁለቱም ጾታዎች ከአንድ እስከ ሶስት ለሚወጡ አትሌቶች የሜዳሊያ ሽልማት እንደሚበረከትና በክልሎች በሚካሄዱት ሩጫዎች ቦንድና ሌሎች ልዩ ሽልማቶች እንደተዘጋጁም አክለዋል።የግድቡ ግንባታ ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ ህብረተሰቡ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል አቶ ዳንኤል ጥሪያቸውን አቅርበዋል።የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በ2004 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን እስካሁን ባለው ሁኔታ የግድቡ ግንባታ ከ64 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። (ኢዜአ) ", "passage_id": "5b584ce21c7725c89a7c4ac11d83b3c7" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ እሁድ ቀን ነው፤ ምሽት አንድ ሰኣት አካበቢ ወደየቤቱ ሊገባ የጓጓን ተሳፈሪ የጫነዉ ታክሲ ትርፍ በተጫኑ ሰዎች ሞልቷል ።ከአጠገቡ ያለን  ክፍት ቦታ የጠቆመኝ ልጅ ጎን ሄጄ ተቀምጫለሁ፤ በግምት 20ዎቹ መጀመሪያ ላይ ያለ ወጣት ነዉ። የስማርት  ስልኩን እየነካካ በቁጭት ሲወራጭ ተመለከትኩት።አዎን፤ በሳምንቱ መጨረሻ የነበረ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ውጤት፣ በመደበው 50 ብር 3 ጨዋታዎችን ገምቷል።ለመቆጨቱ ምክንያት ከሶስቱ በአንዱ መሸነፉ እና ሊያገኝ የጓጓለትን በሺዎች ብር ማጣቱ ስለመሆኑም አጫውቶኛል ።ለሱ ይህ ተግባር፤ ከቀን ገቢው ዘግኖ የሚያስቀርለት ልማዱ ሆኗል።በዚሁ ውርርድ እንደሚሳተፍ የነገረኝ ሌላዉ ስሜ ይቆይ ያለኝ ወጣትም፣ ገንዘብ በያዘበት አጋጣሚ ሁሉ በውርርዱ እንደሚሳተፍ ይናገራል።እርሱ በሚወራረድበት አካበቢ የሚያሸንፉ ወጣቶች ጥቂት መሆናቸዉን ያነሳል።በዚህ ተግባር ውስጥ ግን፤ ሀሳብና ጭንቀት፣ ደግሞም ሲሸነፍ ሌላ ቀን አሸንፋለሁ የሚል እልክ ውስጥ መግባት፣ ሱስ ዉስጥ እንድንገባ ያደርገናል ብሎ ያምናል፤ ይህንን እያወቀም ግን መወራረዱን ቀጥሏል ።“ብር ባገኘሁ ቁጥር እጫወታለሁ፣ ይገርምሀል ከሀያ ብር ጀምሮ ነው የምትቆርጠው፣ ከ20 ብር ጀምሬ እስከ 500 ብር ድረስ ቆርጬ አዉቃለሁ ስንት ለስንት አለቀ እያልክ ለሊት ላይ ብንን የምትለዉ ነገር፤ ከዛ ነገ ስትመጣ ደግሞ የሆነ ብር ሳታገኝ ዛሬ ባላገኛቸዉ ነገ አገኛቸዋለሁ ብለህ ታስባለህ፣  በዚህ ተነሳስተህ ስትቆርጥ ሱስ እየሆነብህ ይመጣል ማለት ነው፤ ገንዘብ ባገኘህ ቁጥር ዛሬ ኳስ አለ እቆርጣለሁ ካልክ ይሄዉ ነገር ሱስ እየሆነብህ ነዉ፣ ኳሱ ቢቆም፣ ኳሱ ይቆማል ሱስ አይሆንም ትላለህ፣ ኳስ ግን ቀጣይነት ያለዉ ነገር ነዉ ስለዚህ ባየህ ቁጥር ደግሞ መቁረጥ አለብህ ማለት ነው፤ ገንዘብ ኪስህ ዉስጥ ካለ በተለይ አያስችልህም”በዚሁ የውርርድ ጨዋታ ውስጥ የሚሳተፉ ወጣቶችም ሆነ የታዳጊዎች ቁጥር ቀላል አለመሆኑን ያነጋገርኳቸዉ ሰዎች ነግረውኛል ።የዉርርድ ተቋማት ተብለዉ ህጋዊ ፈቃድና እዉቅና የተሰጣቸዉ ድርጅቶች፣ የዳበሩ ድረገፆች ያሏቸዉ፣ አማራጭ የአንድሮይድ መተግበሪያን መጠቀማቸዉ እና አለፍ ሲልም ይህ ላልገባቸዉ  በአዲስ አበባ እና በክልሎች የተለያዩ ቦታዎች የመወራረጃ ትኬትን መሸጣቸው ወጣቶች እና ታዳጊዎችን በቀላሉ እንዲይዙ አድርጓቸዋል።የመወራረጃ አማራጮቹም አነስተኛ ከተባለው 10 ብር እስከ ተወራራጁ አቅም ድረስ የሚፈቅደዉ መሆኑ ፣ በሱስ ለሚያዘዉ ሰው የፈለገዉን ያደርግ ዘንድ በር ይከፍታል።የሶሻል ሳይኮሎጂ ባለሙያ እና በሲቪልሰርቪስ ዩኒቨርስቲ አማካሪ የሆኑት ወይዘሮ ቁምነገር ፍቅሬ እንደሚሉት ግን፥ ነገሮች ወደሱስ መቀየራቸውን የምንለካዉ በገንዝቡ ከፍታ አልያም ዝቅ ማለት አይደለም።።“የመጠጥ ሱሰኛ የሆነ ሰው የመጀመሪያ ቀን ስለጠጣ አይድለም ሱሰኛ የሆነው፤ እየደገመዉ ሲሄድ ነው አይደል፤ ልክ ሌላም ሲጋራም ጫትም ብትወስድ እና ልክ እንደዚህ ሁሉ ሱስ ላይ ደረሰ የምንለዉ የቁማር ጨዋታም፤ እየተደጋገመ እየተደጋገመ ይሄድና የሆነ ሰኣት ላይ ሱስ ይሆናል፤ ለምሳሌ አሁን ወጣቱን ብታየዉ እንደአንደኛዉ ስጋት ብታየዉ ስጋት አደርገህ ልታየዉ ትችላለህ፤ አሁን ላይ ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር ተያይዞም ነው ማለት ኢንተርኔት ተደራሽነት በሰፋ ቁጥር የኤሌክትሮኒክ ባንኮች እየሰፉ በመጡ ቁጥር ከማያውቋቸዉ አካላት ጋር ሁሉ ውርርድ እየተካሄደ ነዉ” ይላሉ ወይዘሮ ቁምነገር።በርግጥም በሀገራችን ፈቃድ ተሰጥቷቸዉ ከሚንቀሳቀሱት ከሚያወራርዱ ድርጅቶች በሶስቱ ያደረጉት ቅኝት  ለውርርድ የሚቀርቡት አማራጮች ተዋቂዎቹ ሊጎች ብቻ አይደሉም፤ እንዲያዉም በሀገራችን እምብዛም ታዋቂነትና አድናቂ የሌላቸዉ የጨዋታ አይነቶችም ጭምር እንጂ።የስፖርት ክፍል ባልደረባችን ጋዜጠኛ አላዛር አስገዶም እንደሚለው፥ በሀገራችን ብዙ ተመልካች ያላቸዉ 5ቱ የአዉሮፓ ትልልቅ ሊጎች፣ በእንግሊዝ፣ ስፔን፣ የጣሊያን፣ ጀርመንና ፈረንሳይ የሚከወኑት ነዉ ሲል ይሄዉ የውርርድ እንቅስቃሴ ከዚሁ የወጣ መሆኑን እንኳን ብናይ ግን ከእግርኳስ ጨዋታ ፍቅርና አድናቂነት ያፈነገጠ ለመሆኑ ማሳያ ሊሆነን ይችላል ይላል ።አላዛር አስገዶም፥ የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ለምሳሌ በሳምንት ነዉ ጨዋታዎች የሚደረጉት፤ የአዉሮፓ ጨዋታዎችን የምታካትት ከሆነ ምንአልባት አንድ ክለብ (ቡድን) በሳምንት ሁለት ጨዋታ ሊያደርግ ይችላል እንጂ በየእለቱ ጨዋታ የለም ግን ዝም ብለህ የአለም ሊጎችን ብታይ በየቀኑ የተለያዩ ሊጎች ላይ ጨዋታ ሊኖር ይችላል እና በየእለቱ የሚወራረዱ ሰዎች አሉ የእስራኤል ክለቦችን ማካቢቴልአቪቭ የሚባል ክለብ ብዙ ሰዉ አያውቅም ወይም ቤርሺባህ የሚባል ክለብን ብዙ ሰዉ አያዉቅም ወይ ቱርክ ሁለተኛ ዲቪዚዮን ዉስጥ ያሉ ክለቦችን ብዙ ሰዉ አያዉቅም ግን እነዚህ ክለቦች ጭምር ለውርርድ ሰዎች ይሄኛዉ ክለብ ያሸንፋል ብለዉ ሲወራረዱ እናያለንና በእግር ኳስ ካርታ ውስጥ የሌሉ በቴሌቪዝን ስርጭት የማናያቸዉ በእኛ ሀገር ተወዳጅ ከሆኑ ሊጎች ውጭያሉ ሀገራት የሚገኙ ሊጎች ውስጥ ጭምር ዉርርዱ ይደረጋል፤ አፍጋኒስታን ውስጥ ሳይቀር፤ አፍጋኒስታን በእግር ኳስ የምናዉቀዉ አይደለም በእስያ ዉድድሮች አይሳተፍም፣ በአለም ዋንጫ ተሳትፎ አያዉቅም ግን የአፍጋኒስታን ሊግ ዉስጥ ጭምር ዉርርድ ሲደረግ ታያለህ እና ከስፖርቱ ይልቅ ቁማሩ ያደላል”።በኢትዮጵያ ያለዉ አሁናዊ መልክ አሳሳቢ መሆኑን ከወራት በፊት ያስነበበዉ አለምአቀፉ ተነባቢ መፅሄት ዘ ኢኮኖሚስት ፤ ተይዛለች የሚል ርእስን ሰጥቶት ነዉ ለንባብ ባበቃዉ ዘገባ የዉርርድ ጨዋታ የሚሉት ይሄዉ  ከትንሹ 10 ብር እስከ በርካታ ገንዘቦች የሚመደብበት ዉርርድ በማህበረሰቡ ዘንድ ስር የሰደደ ችግርን ይዞ ስለመምጣቱ ነዉ የሚያነሳው።በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሶሻል ሶሻል ሳይኮሎጂ 2ኛ አመት የፒኤችዲ ተማሪ እና  በሲቪልሰርቪስ ዩኒቨርስቲ አማካሪ የሆኑት ቁምነገር ፍቅሬ እንደሚሉት፥ የድርጊት ተደጋጋሚነት ደግሞ ዉጤቱ የከፋ እዛው አዙሮም  የሚጥል ነው።ቁምነገር ፍቅሬ፥ በእርግጥም ባለሙያዋ እንደሚሉት እንደ ካርታ እና ሌሎችም አይነት ጨዋታዎች ቁማር ከምንለዉ ስማቸዉ በተጓዳኝ በሀዘን ቤት ባላቸዉ ማህበራዊ ፋይዳ  እናዉቃቸዋለን፤ መሰል ዉርርዶችም መነሻቸዉ ምንም ይሁን ምን ተደጋጋሚነታቸዉ ሱስን ይዘዉ መምጣታቸዉ፤ ከግለሰብ እስከሀገር የሚደርስ ቀዉስን መጥራታቸዉ አይቀርም ።የዘ ኢኮኖሚስቱ ዘገባ እና ሌሎችም ስለጉዳዩ የሚያዉቁ ይህንኑ አይነት እንቅስቃሴ ቁማር ነዉ ሲሉት፤ ስለመሰል ጉዳዮች ይሁንታዉ የሚጠበቅ የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን  የዉርርድ ጨዋታ ነዉ በሚል ህጋዊ ፈቃድ እና እዉቅና ሰጥቶታል።አሁን ወደ 22 የሚጠጉ ድርጅቶችም እየተንቀሳቀሱ ቆይተዋል፤ አሁን አሁን የማህበራዊ ቀዉሱ ብልጭታዎች መታየት ጀምረዋል። ለመሆኑ የሌሎች አፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ ምንድን ነው፤ ጉዳዩ ከማህበራዊ ቀዉስ በሀገሪቱ እግርኳስ ላይ የሚያሳርፈዉ አሉታዎ ጫናስ የት ይደርሳል ፤ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሎተሪስ ምላሽስበቀጣይ ተከታታይ ዘገባዎችን የምንሰራ ይህናል ።በፀጋዬ ወንድወሰን ", "passage_id": "c18ece879e67d8aa90c2b4168db3784f" } ]
6529926190fe641603b75c1cbfe5b70c
990c386647d14237d680e961d3eda8ef
የኦሊምፒክ ችቦው ቅብብሎሽ ደማቅ ጉዞ
4ተኛው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ችቦ መለኮስ ሥነ ሥርዓት ከትናንት በስቲያ በመቖለ ሮማናት አደባባይ በርካታ የከተማው ነዋሪዎች በተገኙበት ተከናውኗል። በሥነ ሥረዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል፣ ለቶኪዮ ኦሊምፒክ የትግራይ ክልል በተለያዩ ስፖርቶች ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን በማስመረጡ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል የትግራይ ክልል በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን የሚወክሉ በአትሌቲክስ 10 እና በብስክሌት 1 አትሌት ማስመረጥ መቻሉን ያስታወሱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ክልሉ ስፖርቱን ለማጠናከርና የኦሊምፒክ ቡድኑን ለመደገፍና የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ከኦሊምፒክ ኮሚቴው ጎን እንደሚቆም በማረጋገጥ ከወዲሁ ለኦሊምፒክ ቡድኑ መልካም ዕድል ተመኝተዋል።የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ የቶኪዮ 2020 ብሔራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አባዱላ ገመዳ በትግራይ የተለኮሰው የኦሊምፒክ ችቦ ሥነ ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ‹‹ትግራይ ብዙ ጀግኖችን አፍርታለች፣ በስፖርቱም በቀጣይ በተለያዩ ስፖርቶች አገርን የሚወክሉ አትሌቶች ማፍራት ይጠበቃል›› ብለዋል አቶ አባዱላ ንግግራቸውን በድንገት ገታ አድርገውም በቶኪዮ 2020 በብስክሌት ኢትዮጵያን በብቸኝነት የምትወክለው የትራንስ ኢትዮጵያ ክለብ ብስክሌት ጋላቢዋን ሰላም ዓመሀን ወደ መድረክ በመጥራት ‹‹በብቸኝነት ኢትዮጵያን በመወከልሽ ትልቅ ደስታ ተሰምቶኛል ከህዝብ በስጦታ የተበረከተልኝ ነው›› በማለት ከአንገታቸው የወርቅ ሀብል አውልቀው ሽልማት አበርክተውላታል።በችቦ መለኮስ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ችቦውን ከትግራይ ክልል የተረከቡት የጋምቤላ ክልል አፈጉባኤ አቶ ላክደር ላባክ በበኩላቸው ‹‹የኦሊምፒክ ቡድኑን ለመደገፍ በቀጣይም በስፖርቱ መሠረተ ልማት ላይ የበኩላችንን ለመወጣት እድሉን በማግኘታችን ደስተኞች ነን›› በማለት ተናግረዋል 5ተኛው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ችቦ መለኮስ ሥነ ሥርዓት መጋቢት 6/2012 በጋምቤላ ክልል የሚከናወን ሲሆን የክልሉ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ታይዶር ቻምባንግ መቖለ በነበረው የችቦ መለኮስ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው ችቦው ሲረከቡ ‹‹በስፖርት ህብረተሰቡን ተሳታፊ ማድረግ እንዴት እንደሆነ ከትግራይ ክልል ትምህት ወስደናል›› ብለዋል። ለቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ቡድን እደክልል በተገቢው መንገድ እንደሚደግፉም አብራርተዋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ከጀግናው አትሌት ሻበል ምሩፅ ይፍጠር ልጅና የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ቢኒያም_ምሩፅ ጋር መገናኘታቸውን ከኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዝግጅትን በተለየ መልኩ ለማከናወንና ለትውልድ የሚተላለፍ ዘመናዊ የኦሊምፒክ አካዳሚን የመገንባት ዕቅድ በመያዝ የብሔራዊ ዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ ሥራዎችን ከጀመረ ሰንብቷል። ኮሚቴው ሕዝቡን በነቂስ የሚያሳትፍ የመጀመሪያ መርሐግብሩን የካቲት 8 ቀን 2012 ዓ.ም. በመስቀል አደባባይ የኦሊምፒክ ችቦ በመለኮስ መነሻውን አዲስ አበባ አድርጎ ወደ ሌሎች ክልሎች እንዲዞር በማድረግ መጀመሩ ይታወሳል። የኦሊምፒኩን ችቦ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የተረከበ ሲሆን ከድሬዳዋ ተከትሎ ሶማሌ፣ ትግራይ፣ ጋምቤላ፣ አፋር፣ ሐረሪ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ላይ መጨረሻውን ያደርጋል። አዲስ ዘመን መጋቢት 1/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28830
[ { "passage": "የዓለም ትልቁ ስፖርታዊ ውድድር ኦሊምፒክ ከመካሄዱ አንድ ዓመት አስቀድሞ ይካሄዳል። በተለያዩ ክፍለ አህጉራት የሚካሄደው ይህ ውድድር እንደ ኦሊምፒክ የሚታይ ሲሆን፤ የአህጉሩን አገራት በተለያዩ ስፖርቶች ያወዳድራል። በአፍሪካም እ.ኤ.አ 1965 ለመጀመሪያ ጊዜ ሲካሄድ፤ በየአራት ዓመቱ እየተዘጋጀ አሁን 12ኛ ጊዜ ላይ ደርሷል። ውድድሩ እ.ኤ.አ እስከ 2012 የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በሚል ሲጠራ ቢቆይም፤ አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው ጉባኤ የአፍሪካ ጨዋታዎች በሚል እንዲሻሻል ተደርጓል። በአፍሪካ ሕብረት፣ በአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበራት እንዲሁም በአፍሪካ ስፖርት ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አስተባባሪነት ይካሄዳል። የአፍሪካ ሕብረት የውድድሩ ባለቤት ሲሆን፤ የኦሊምፒክ ኮሚቴዎቹ ማህበር ቴክኒካዊ ጉዳዮችን በመምራት እንዲሁም ኮንፌዴሬሽኑ ከገንዘብ እና ከስፖንሰሮች ጋር የተያያዘውን ጉዳይ በማስተባበር ተሳትፏቸውን ያደርጋሉ። በዓለም አቀፉ\nየኦሊምፒክ ኮሚቴ በበላይነት የሚመራው አህጉር አቀፉ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ በኮንጎ ብራዛቪል ነበር የተካሄደው። በዚህ ውድድር ላይ ተሳታፊ የሚሆኑት የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አባል አገራት ሲሆኑ፤ በአፍሪካ አቀፉ ውድድር ላይም 53ቱም አባል አገራት ተካፋይ ነበሩ። የኦሊምፒክን ጽንሰ ሐሳብ ተከትሎ የሚካሄደው ውድድሩ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነትን ይቃወማል። ከዚህ ቀደም በደቡብ አፍሪካ በነበረው የአፖርታይድ ሥርዓት እንዲሁም በሞሮኮ ተከስቶ በነበረው ፖለቲካዊ ቀውስ ምክንያት አገራቱን ከተሳታፊነት አግልሎም ነበር። የዘንድሮው ውድድር በሞሮኮዋ ራባት\nየሚካሄድ ሲሆን፤ 53አገራት በ23 የስፖርት ዓይነቶች ብሔራዊ ቡድኖቻቸውን ያሳትፋሉ። በቀጣዩ ወር\nየሚጀመረው ውድድሩ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱን በንጉሥ ሞሐመድ 6ኛ ስታዲየም እንደሚደረግ ይጠበቃል። አገሪቷ በአጠቃላይ ለውድድር እንዲሁም ለልምምድ የሚሆኑ 13 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችንም አዘጋጅታ ተሳታፊዎቿን በመጠባበቅ ላይ\nትገኛለች። በዚህ ውድድር ተሳትፎ በርካታ ሜዳሊያዎችን በማስቆጠር በሰንጠረዡ አናት የተቀመጠችው ግብጽ 1ሺ362 ሜዳሊያዎችን ሰብስባለች። ሁለተኛዋ አገር\nናይጄሪያ በበኩሏ 1ሺ199 ሜዳሊያዎች አሏት። ደቡብ\nአፍሪካ ደግሞ በ967 ሜዳሊያዎች ሦስተኛ ደረጃ\nላይ ትገኛለች። ስምንተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ኢትዮጵያ 122 ሜዳሊያዎች ሲኖሯት፤ ከእነዚህ መካከል 39ኙ የወርቅ፣ 39ኙ\nየብር እንዲሁም 52 ቱ የነሐስ ሜዳሊያዎች ናቸው። ከአራት ዓመታት በፊት\nበኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ ኢትዮጵያ ኬንያን በመከተል ስምንተኛ ሆና ያጠናቀቀች ሲሆን፤ 6 የወርቅ፣ 5 የብር እና 6 የነሐስ በጥቅሉ 17 ሜዳሊያዎችን ነበር ያስመዘገበችው። ኢትዮጵያ በዘንድሮው ውድድር በ13 የስፖርት ዓይነቶች የምትሳተፍ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nአስታውቋል። የተወሰኑ ስፖርቶች ዝግጅታቸውን ሲጀምሩ ሌሎች ደግሞ ተሳታፊ ስፖርተኞቻቸውን ለመምረጥ ሻምፒዮናዎችን እያካሄዱ ይገኛሉ። የስፖርት ዓይነቶቹም፤ አትሌቲክስ፣ ብስክሌት፣ ቦክስ፣ ካራቴ፣ ወርልድ ቴኳንዶ፣ ቼስ፣ ክብደት ማንሳት፣ የውሃ ስፖርቶች፣ ጂምናስቲክ፣ ቅርጫት ኳስ፣ ባድሜንተን፣ ጠረጴዛ ቴኒስ እና ሜዳ ቴኒስ ናቸው። ቀድመው ወደ ዝግጅት ከገቡት ስፖርቶች መካከል አንዱ ኢትዮጵያ የምትታወቅበትና ውጤታማ የሆነችበት የአትሌቲክስ ስፖርት አንዱ ነው። በዚህ ውድድር የሚሳተፉ አትሌቶች በግንቦት ወር የተመረጡ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ሆቴል ተቀምጠው ዝግጅት በማድረግ ላይም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር ከ100-10ሺ\nሜትር ባሉት የሩጫ እና የሜዳ ተግባራት ስትካፈል፤ በጥቅሉ105 አትሌቶች ተመርጠዋል። አትሌቶቹ ሊመረጡ የቻሉትም ከወራት በፊት በተካሄደው 48ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታወቋል። ሌላኛው ዝግጅቱን አስቀድሞ የጀመረው ስፖርት ቦክስ ሲሆን፤ በ7 ወንድ\nእና 2 ሴት ቦክሰኞች ብሔራዊ ቡድኑ እንደሚወከል ከኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ይጠቁማል። በወንዶች ምድብ የተመረጡት ቦክሰኞች፤ በ49፣56፣ 60፣ 64፣ 69፣ 75 እና 81 ኪሎ ግራሞች በውድድሩ ላይ ይሳተፋሉ። በሴቶች በኩል ደግሞ በ48 እና\n51 ኪሎ ግራሞች ተካፋይ ይሆናሉ። በየዓመቱ በአራት ዙሮች ከሚካሄደው የኢትዮጵያ ክለቦች ሻምፒዮና የተመረጡት ቦክሰኞቹ በሦስቱ ዙር የተሻለ ብቃት በማሳየታቸው የተመረጡ መሆናቸውም ታውቋል። ሌላኛው ተሳትፎ የሚደረግበት ስፖርት ብስክሌት፤ በመቀሌ ከሰኔ 19- 22 በተካሄደው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ተመርጠዋል። እስከ ሐምሌ አንድ ቡድኑን የሚቀላቀሉት ብስክሌተኞች ታውቀው ወደ ዝግጅት የሚገቡ ሲሆን፤ በሁለቱም ፆታ በሚካሄዱት ሁሉም የውድድር ዓይነቶች ለመሳተፍ ማቀዱን ፌዴሬሽኑ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ገልጿል። በክብደት ማንሳት ስፖርትም በተመሳሳይ ተካፋይ የሆኑ ስፖርተኞች የሚመረጡበት አገር አቀፍ ሻምፒዮና ተካሂዷል። በወንዶች ከ55-102 ኪሎ\nግራም በሴቶች ደግሞ ከ45-71 ኪሎ\nግራም በተካሄደው በዚህ ውድድር በሁለቱም ፆታዎች አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ይመረጡበታል። አዲስ ዘመን ሀምሌ\n15/2011 ", "passage_id": "ef46719f090fdff1a8afb7fbe0c9c9dd" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳ የቶኪዮ 2021 ኦሊምፒክ ከመካሄዱ ወራትን አስቀድሞ ዝግጅት መጀመሩ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ የሚያደርግ መሆኑ ተገለጸ። በኦሊምፒክ መድረክ ሃገራቸውን ለወከሉ አትሌቶች የተካሄደው የምስጋና መርሃ ግብር፤ ለመጪው ኦሊምፒክ ተሳታፊዎች መነሳሳትን እንደሚፈጥርም ተጠቆመ፣ ከዚህ ቀደም ይደረግ ከነበረው በተለየ ሁኔታ ከወራት በፊት ካምፕ በመግባት የረጅም ጊዜ ዝግጅት ማድረግ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን የተሻለ ውጤት እንዲያመዘገብ ያስችላል ተብሏል። በ5ሺ ሜትር ሃገሩን ለመወከል በቡድኑ የተካተተው አትሌት ጫላ ከተማ፤ ብሄራዊ ቡድኑ ዝግጅቱን ከጀመረ አንድ ወር እንዳስቆጠረ ይገልጻል። ማረፊያውን በጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል ያደረገው ቡድኑ በሰንዳፋ፣ አዲስ አበባ ስታዲየም እና በቃሊቲ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን፤ በውድድሩ ወቅት በጃፓን የሚኖረው የአየር ሁኔታ ሞቃታማ ሊሆን ስለሚችል ከባድ ሊያደርገው ይችላል ከሚለው ግምት ባሻገር መልካም ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ያረጋግጣል።እንደ አትሌቱ ገለጻ፤ ከዚህ ቀደም ከወራት በፊት ካምፕ በመግባት ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ተደርጎ አያውቅም። ኢትዮጵያ የምትታወቀው በቡድን ስራ ቢሆንም በዝግጅት ወቅት ተለያይቶ መስራት ውጤት እንዲጠፋ አድርጎት ቆይቷል። አሁን ግን ለረጅም ወራት አትሌቱ በአንድ ተሰባስቦ መስራቱ አትሌቶች እንዲግባቡና ለቡድን ስራም የሚያግዝ መሆኑን ያምናል። በአሰልጣኞችና በፌዴሬሽኑ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑም የተሻለ ውጤት ይመጣል የሚል እምነቱንም አትሌቱ ያንጸባርቃል። ከዚህ ባሻገር ቡድኑ ኮቪድ 19ን በመከላከል ረገድም አስፈላጊውን ሂደት እየተከተሉ መሆኑን አትሌት ጫላ ይጠቅሳል። ያረፉበት ሆቴል ከአትሌቶች ውጪ ሌሎች ሰዎች የማይገለገሉበት ሲሆን፤ በልምምድና በሌሎች እንቅስቃሴዎች ውስጥም ንጽህናቸውንና ርቀታቸውን ከመጠበቅ ጎን ለጎን በጤና ባለሙያዎችም ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ሲል ያብራራል። ‹‹የባዶ እግር ትሩፋቶች›› በሚል በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት በቅርቡ የተካሄደው የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር፤ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ተሳታፊ ለሚሆኑ አትሌቶች መነሳሳትን እንደሚፈጥርም በባለሙያዎች ታምኖበታል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በተከሰተው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ኦሊምፒክ ለአንድ ዓመት መራዘሙ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎም ለቶኪዮ 2021 ኦሊምፒክ አትሌቶችና አሰልጣኞች ከወዲሁ ዝግጅት መጀመራቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ ጠቁማለች። ለብሄራዊ ቡድን የተመረጡት አትሌቶች ለሁለት ተከፍለው በአሰለፈች መርጋ እና በጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል መቀመጫቸውን በማድረግ ዝግጅት እያደረጉ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ፌዴሬሽኑ ለቀደሙት የኦሊምፒክ ተሳታፊዎችና ባለድል አትሌቶች እንዲሁም ባለሙያዎች ማበረታቻ ማዘጋጀቱ፤ በቡድኑ ለታቀፉ አትሌቶች ሞራል እንደሚሆን ይጠበቃል። በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለአትሌቶችና ቤተሰቦቻቸው ሽልማት ያበረከቱት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ ዘመኑ እንዳሁኑ ባልሰለጠነበትና መሰረተ ልማትም ባልተሟላበት ወቅት ኑሮ ከሩጫ ጋር የተያያዘ በመሆኑ አትሌቶች ስልጠናም ሳያስፈልጋቸው በኦሊምፒክ ሮጠው ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል። አሁን ግን ጊዜው እንደዚያ አለመሆኑን ጠቅሰው፣ አትሌቶች ለቶኪዮ ኦሊምፒክ በደንብ መዘጋጀት ይኖርባቸዋል ብለዋል። በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶች ሆቴል ቢገቡም ጊዜው እጅግም ሩቅ ባለመሆኑ በደንብ መጠበቅ እንዳለባቸውም ነው ያሳሰቡት። መጪው ኦሊምፒክም በሽልማት መድረኩ ስማቸው የተነሳው አትሌቶች ገድል የሚታደስበት ሊሆን ይገባል ያሉት ፕሬዚዳንቷ፣ ለቶኪዮ በሁሉም መንገድ መዘጋጀት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል። ኢትዮጵያንና አፍሪካን ከፍ ለማድረግና ቶኪዮ ላይ ያሸነፈውን የአበበ ቢቂላን ድል ለማደስ፤ የሚመለከታቸው ሁሉ አትሌቶችን በማዘጋጀትና በመደገፍ ጥረት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አስታውቀዋል። በቶኪዮ 2021 በአሸናፊነት በተመሳሳይ መርሃ ግብር ለመገናኘት ፕሬዚዳንቷ ምኞታቸውን ገልጸዋል። የቶኪዮ ኦሊምፒክ መራዘም ለበጎ መሆኑን የሚያመላክቱት ደግሞ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሰው ናቸው። የቶኪዮ 2021 ድል ከዚህ ቀደም ከነበረው እጥፍ ድርብ እንደሚሆን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ ለአትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ አመራሮችና በስፖርቱ ላይ ለሚሰሩት ሁሉ የምስጋና መርሃ ግብሩ የብርታት ስንቅ እንደሚሆናቸው ነው የገለጹት። ከአንድ ዓመት በፊት በቶኪዮ በተካሄደ በሻምበል አበበ ቢቂላ ድል የ20 ኪሎ ሜትር የማስታወሻ ሩጫ ላይ የኢትዮጵያ ዝግጅት መልካም እንዳልነበር ለመታዘብ ተችሏል። በወቅቱ በጃፓን የተገኙ የፌዴሬሽኑ አመራሮች ልምድና አሰራር ተምረው መመለሳቸውን ተናግረው፣ በዚሁ መሰረት በመስራት የጀግና እና የይቻላል ስነልቦና የተላበሰ ህዝብ ያለባት ሃገር መሆኗ ዳግም እንደሚታይም ያላቸውን ተስፋ አንጸባርቀዋል።", "passage_id": "0c246c95c710d21f1133b25ca0340f7b" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳ ጃፓን አስተናጋጅ የሆነችበት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ሊካሄድ 192 ቀናት ብቻ ይቀሩታል። ኢትዮጵያም ለዚህ ኦሊምፒክ ከዚህ ቀደም ተደርጎ በማያውቅ ሁኔታ ስምንት ወራትን አስቀድማ ተሳታፊ አትሌቶቿ ወደ ዝግጅት እንዲገቡ አድርጋለች። የምትሳተፈው በአትሌቲክስ፣ ቦክስ እና ወርልድ ቴኳንዶ ስፖርቶች ቢሆንም፤ በተለይ ታዋቂ የሆነችበትና ውጤትም የምታስመዘግብበት አትሌቲክስ ዝግጅቱን አጠናክሮ ቀጥሏል። በመካከለኛና ረጅም ርቀት ለሚካሄደው ውድድር የተመረጡት አትሌቶች ለሁለት ተከፍለው በአሰለፈች መርጊያ እና ሰንዳፋ በሚገኘው ጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል መቀመጫቸውን አድርገዋል። አጠቃላይ እየተካሄደ ያለው ዝግጅት ምን ይመስላል በሚለው ላይም አዲስ ዘመን ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አትሌቲክስ ክለብ ዋና አሰልጣኝና የቶኪዮ ኦሊምፒክ ረጅም ርቀት ዋና አሰልጣኝና የአሰልጣኞች አስተባባሪ ኮማንደር ሁሴን ሸቦ ጋር ቆይታ አድርጓል። በግዙፏ አህጉር ለሁለተኛ\nጊዜ ጃፓን የምታዘጋጀው\nይህ ኦሊምፒክ የኮቪድ\n19 ቫይረስ በመላው ዓለም\nባሳደረው ተጽእኖ ምክንያት\nለአንድ ዓመት ሊራዘም\nችሏል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ\nብሄራዊ ቡድንም \nዝግጅቱን አቋርጦ በመቆየት ካለፈው ህዳር/2013 ዓ.ም መጀመሪያ አንስቶ ተሰባስቧል። አሰልጣኝ ሁሴን ሸቦም አሰልጣኞችና አትሌቶች በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት በሆቴል ተሰባስበው ስልጠና ላይ እንደሚገኙ ይገልጻሉ። በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኩልም የሚደረግላቸው ክትትልና ቁጥጥርም በመልካም ሁኔታ እየሄደ መሆኑንም ያመላክታሉ። አሰልጣኝ ሁሴን እንደሚሉት፤ በአሰልጣኞች ቡድን በተያዘው እቅድ መሰረት ስልጠናው የሚሰጠው በምዕራፍ ተከፋፍሎ ነው። በሂደት አትሌቶቹ ለውድድር ብቁ መሆናቸውና የሚያስመዘግቡት ብቃትም እየተመዘነ በመጨረሻ በየርቀቱ አንድ ተጠባባቂ ብቻ በመያዝ 16 አትሌቶች የሚቀሩ ይሆናል። የቡድኑ አባላት አትሌቶች የሚመረጡት ከሁሉም የሀገሪቷ አቅጣጫ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከትግራይ ክልል የተመረጡ አትሌቶች በወቅቱ በነበረው ሁኔታ ክለቡን መቀላቀል እንዳልቻሉና ይህም በስልጠናው ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ሊያሳርፍ ይችላል የሚል ስጋት አሳድሮ ነበር ይላሉ። አሰልጣኞች በወቅቱ አትሌቶቹ ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ሙከራ ማድረጋቸውን አስታውሰው፣ በክልሉ የስልክ አገልግሎት በመቋረጡ ምክንያት መገናኘት አለመቻሉ በዝግጅቱ መጀመሪያ ችግር አጋጥሞ እንደነበር ይናገራሉ። እንደ አሰልጣኙ ገለጻ፤ ኦሊምፒኩ በሚካሄድበት በፈረንጆቹ መጋቢት ወር በጃፓን የሚኖረው የአየር ሁኔታ ሞቃታማ እንደሚሆን ይጠበቃል። በመሆኑም ይህንን ያገናዘበ ስልጠና ከመስጠት አንጻር እየተሰራ ነው። ከዚህ ጎን ለጎን ኦሊምፒኩ ከመካሄዱ አስቀድሞ ለኦሊምፒኩ አጋዥ ሊሆኑ የሚችሉ ውድድሮች ይኖራሉ። እንደ ዳይመንድ ሊግ ያሉ ውድድሮች በተለይ ጠቃሚ ቢሆኑም፤ አሳዛኝ በሆነ መልኩ ዘንድሮ እንደ ቀደሙት ጊዜያት ውድድሮችን በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። ለአብነት ያህልም የዓለም ሀገር አቋራጭ ቻምፒዮና የተሰረዘ ሲሆን፤ የዓለም የቤት ውስጥ ውድድሮችም በተመሳሳይ አይካሄዱም። በስፖርት ቤተሰቡም በኩል ከቀደመው ጊዜ በተለየ መቀዛቀዝ በመስተዋሉ ምቾት የሚነሱ ጉዳዮች መኖራቸውን ነው አሰልጣኙ የሚጠቁሙት። የሆነ ሆኖ ግን በዳይመንድ ሊግ ውድድሮች አትሌቶችን በማሳተፍና ሚኒማ እንዲያሟሉ በማድረግ ኢትዮጵያ የለመደቻቸውን የወርቅ፣ ብርና ነሃስ ሜዳሊያዎች ለማስመዝገብ ዝግጅቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ይላሉ። አትሌቲክስ የረጅም ጊዜ ስራን የሚፈልግ እንደመሆኑ ስምንት ወራትን ቀደም ተብሎ ዝግጅት መጀመሩ መልካም መሆኑንም ነው አሰልጣኙ ያብራሩት።ባለፉት\nኦሊምፒኮች አትሌቶች በዝግጅት\nላይ ሆነውም ሚኒማ\nእንዲያሟሉ መደረጉ ወጣ\nገባ ማለትን የሚያስከትልና\nስልጠናው ላይም ተጽእኖ\nየሚያደርስ መሆኑን በመጥቀስ\nየስፖርት ቤተሰቡ ስጋቱን\nይጠቅሳል የሚሉት አሰልጣኝ\nሁሴን፣ ለሁሉም አትሌቶች\nየሚሆኑ ውድድሮችን በተመሳሳይ\nጊዜ ማግኘት እንደማይቻል\nነው የሚናገሩት። ለዚህ\nየተቀመጠው መፍትሄ አትሌቶች\nውድድር ሲኖራቸው ቡድኑ\nካለበት ካምፕ ወደ\nውድድሩ ስፍራ ተጉዘው\nከተካፈሉ በኋላ በቀጥታ\nወደ ካምፕ እንዲመለሱ\nማድረግን መሆኑን ያመለክታሉ።\nከዚህ ቀደም በተካሄዱ\nኦሊምፒኮችም መሰል ልምዶች\nእንዳሉ አሰልጣኙ ያስገነዝባሉ።\nውድድሩ\nየአትሌቶች ብቃት የሚለካበት\nመሆኑን ጠቅሰው፣ ቡድኑ\nላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ\nእንዳይኖር ይሰራል ብለዋል።\nየኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nእና አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም\nበዚህ ረገድ እገዛ\nእንደሚያደርጉም ነው ተስፋቸውን\nያመለከቱት። ማጣሪያን\nበተመለከተም አሰልጣኝ ሁሴን\nከዚህ ቀደም በሄንግሎ\nበሚደረገው የሰዓት ማጣሪያ\nሚኒማውን ማሟላት የቻሉ\nአትሌቶች ይመረጡ እንደነበር\nያስታውሳሉ። በዚህ ዝግጅት\nላይ ግን ተጨማሪ\nማጣሪያ ተዘጋጅቶ የመጀመሪያው\nየዝግጅት ምዕራፍ እንደተጠናቀቀ\nማጣሪያ ማካሄድ ቢቻልና\nአጠቃላይ የቡድን ዝግጅቱ\nከተጠቃለለ በኋላ የተለመደው\nየሄንግሎ ማጣሪያ ቢከተል\nመልካም እንደሚሆንም አሰልጣኝ\nሁሴን ሃሳባቸውን ያቀርባሉ።\nይህንኑ ሃሳብ ለኦሊምፒክ\nኮሚቴና ለፌዴሬሽኑ በማቅረብ\nበጎ ምላሽ እንደሚያገኙም\nያላቸውን ተስፋ ይገልጻሉ።\nአትሌቶች\nበብዛት ውጤት የማያገኙ\nከሆነ በሄንግሎ ብቻ\nተመርጦ በኦሊምፒክ ላይ\nውጤታማ ለመሆን ይቻላል\nማለት አስቸጋሪ ነው\nያሉት አሰልጣኙ፣ ተደጋጋሚ\nልምድና ተደጋጋሚ ውድድር\nበማድረግ ከዚያ መካከል\nነጥረው የወጡትን አትሌቶች\nበአካል ብቻም ሳይሆን\nበስነ ልቦና ረገድ\nኃላፊነትና የሀገር አደራን\nመወጣት እንዲችሉ ለማድረግ\nዘንድሮ ተጨማሪ ውድድሮች\nለማድረግ መታቀዱን ይገልጻሉ።\nእንደሚታወቀው\nአትሌቶች በግል ውድድሮቻቸው\nላይ ይልቁንም በጎዳና\nላይ ውድድሮች ትኩረት\nማድረጋቸው የሀገሪቷ የመም\nውጤቶች እንዲዳከሙ አድርጓል።\nከዚህ ቀደም በተካሄዱ\nኦሊምፒኮች ላይም ይኸው\nምልክት መስተዋሉ በዚህ\nኦሊምፒክም ተመሳሳይ ስጋት\nአሳድሯል። በረጅም ርቀት\nአሰልጣኝነት ከፍተኛ ልምድ\nያካበቱት አሰልጣኝ ሁሴን\nሸቦ ግን በቶኪዮ\nኦሊምፒክ ውጤት ከማስመዝገብ\nአንጻር ስጋት እንደሌላቸው\nነው የሚገልጹት። በእርግጥ\nበሀገሪቷ የኦሊምፒክ ተሳትፎ\nትልልቅ ውጤት የተመዘገበባቸው\nየሲድኒ እና ቤጂንግ\nኦሊምፒኮች ናቸው። አሁን\nዋነኛው ነገር አትሌቶችን\nከጎዳና ላይ ውድድሮች\nማቀብ አስፈላጊ መሆኑ\nነው። በእርግጥ ይህም\nቀላል ስራ ሳይሆን\nከአትሌቶችና ከማናጀሮቻቸው ጋር\nአስቸጋሪ ትንቅንቅ ማድረግን\nይጠይቃል። ነገር ግን\nፌዴሬሽኑ የሚረዳቸው ከሆነ\nበመተጋገዝ አትሌቶችን ከጎዳና\nወደ መም መመለስ\nይቻላል። ይህ ከሆነም\nስጋት እንደማይኖርና ብቃት\nያላቸው አትሌቶች መኖራቸውን\nይጠቁማሉ። በቅርቡ የዓለምን\nክብረወሰን የሰበሩ እና\nአሁንም መስበር የሚችሉ\nጠንካራ አትሌቶች እንዳሉም\nያረጋግጣሉ። በብዙዎች\nዘንድ ያደረው ስጋት\nሊከሰት የሚችለው ካልተሰራ\nእና ባለመስማማት ብቻ\nመሆኑንም ጠቅሰዋል። አትሌቶቸና\nአሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና ፌዴሬሽኑ\nእንዲሁም ኦሊምፒክ ኮሚቴው\nበስምምነትና በመተባበር ከሰሩ\nውጤት በእጃቸው ላይ\nመሆኑንም ይጠቅሳሉ። ሃሳባቸውን\nለማጠናከርም በሪዮ ኦሊምፒክ\nየተጠበቀው ውጤት ላለመመዝገቡ\nምክንያት የሆነው በፌዴሬሽኑ\nውስጥ የነበሩ ሁኔታዎች\nመሆናቸውን አስታውሰዋል። ሁሉም\nሀገራት የተሻለ ዝግጅት\nአድርገው በውድድሩ እንደሚካፈሉ\nእርግጥ ቢሆንም ቡድኑ\nአሁን ባለበት ሁኔታ\nግን ጥሩ የውጤታማነት\nእድል ያለው ከመሆኑም\nባለፈ እስካሁን ከተመዘገቡ\nከፍተኛ ድሎች ያልተናነሰ\nውጤት ሊመዘገብ የሚችልበት\nእድል መኖሩን ይጠቁማሉ። አጀማመሩ\nመልካም የሚባል ከመሆኑም\nባሻገር አትሌቶች ከጎዳና\nላይ ውድድሮች ታቅበውና\nየግለሰቦች ጣልቃ ገብነት\nሳይኖር የሚቀጥል ከሆነ\nእንዲሁም በወጣው ዕቅድ\nመሰረት ስልጠናው ወቅቱን\nጠብቆ ከተካሄደ የተሻለ\nውጤት ሊመዘገብ እንደሚችልም\nነው አሰልጣኙ ተስፋቸውን\nየገለጹት። ከዚህ ቀደም\nየነበረው አትሌቶች በሌሎች\nውድድሮች ላይም ተሳትፎ\nሲያደርጉ ቆይተው ውድድሩ\nሲቃረብ ጉዳት ማስተናገድና\nለህመም መዳረግ ነው\nይላሉ። እንደ አሰልጣኙ ገለጻ፤ ከኮቪድ 19 ጋር በተያያዘ ስልጠናው በጥንቃቄ እየተሰጠ ሲሆን፤ የፌዴሬሽኑ ሃኪሞችም ጥሩ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ላይ ናቸው። በዝግጅቱ ማጠናቀቂያ ምናልባትም ቫይረሱ የሚገኝባቸው አትሌቶች ሊኖሩ ይችላሉ። በዚህ ረገድ በአሰልጣኞች የተያዘው እቅድ ከወትሮው ለየት ያለ ነው። ይኸውም ቀድሞ በተወዳዳሪነት ይያዙ የነበሩት አራት አትሌቶች ቢሆኑም አሁን ግን አምስት አትሌቶችን በመያዝ፤ ውድድሩ ሲደርስ ቫይረሱ ተገኝቶባቸው የሚቀሩ አትሌቶች ቢኖሩ በምትካቸው የሚገቡ ይሆናል። የቫይረሱ ባህሪ አስቸጋሪና ሊገመት የማይችል በመሆኑ ወደ ጃፓን የሚኖረው ጉዞ ቀናትን አስቀድሞ እንደመሆኑ ከዚህ ነጻ ሆነው እዚያ ከደረሱ በኋላ የሚያዙ ሊኖሩ ስለሚችሉም ሁለት ተጠባባቂዎችን ይዞ መጓዙ የተሻለ ይሆናል።", "passage_id": "6f952b5709aad40109b500b153b9a670" }, { "passage": "ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ከመዝናኛነት ባሻገር ጥልቅ የሃገር ፍቅር መውጫ የጦር አውድ መሆኑን በርካቶች ሲናገሩ ይደመጣሉ። «የአትሌቶች ሀገር» ሲል አለም የመሰከረላት ኢትዮጵያችን ለዚህ ንግርት ማረጋገጫ በመሆን ትጠቀሳለች። በአትሌቶቿ በአለም አቀፍ መድረኮች ዘመን ተሻጋሪ የድል ታሪክ በማስመዝገብ አለም የአትሌቶች ሃገር የሚል ተቀጽላን አክሎ እንዲጠራት አድርጓል። ኢትዮጵያን በጀግንነት ለማስጠራት እነዚህ ጀግና አትሌቶች አድካሚና ፈታኝ መንገድ መጓዝ ግድ ይላቸዋል። ፈተናዎቹንም በአሸናፊነት በጣጥሶ ማለፍ ይጠይቃል። ከአትሌቶቹ ጽናት በተሞላው የድል መዳረሻ ጀርባ «የሃገር ክብር»የሚባል ጥልቅ የሃገር\nፍቅር ብርታትና ጉልበት ሲሆናቸው ታዝበናል። በአትሌቶቹ ድል በአለም ፊት አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ቀይ ሰንደቅ አላማ ከፍ ብሎ ተውለብልቧል።\nየድሉ ባለቤት የሆኑት አትሌቶቻችን የሃገር ፍቅር፣ ክብርና ነጻነት ትርጓሜን ያዘለው ሰንደቅ ከፍታ፤ጥልቁን የሃገር ፍቅር ለመግለጽ\nእንባቸውን መገደብ በተሳነው ሁናቴ ሲገልጹ ተመልክተናል። የኢትዮጵያ ክብርና አርማ በሆነው ኃይሌ ገብረስላሴ፣ በእንስቷ ንግስታችን ደራርቱ ቱሉ\nየ2001 የሲድኒ ኦሎምፒክ የዘላለም ምስክር ናቸው። በተለያየ የእድሜ ክልል የሚገኘው ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የአትሌቶቹ በጥልቅ\nየሃገር ፍቅር ተሞልቶ ድልን የመሻት እሩጫን በማበረታታትና በማገዝ ረገድ ሚናውን ይወጣል። በድሉ ግኝት በሃገር ፍቅር ስሜትና አብሮነት ደስታውን ያጣጥማል። በአንድነት ብሮ ወሸባዬን\nይጨፍራል። በኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ቀለም ሰንደቅ አላማውን በክብር ከፍ አድርጎ በአንድነት ይሰቅላል። በስፖርቱ\nድል የሃገር አሸናፊነትን ስሜቱን ይወጣል። በአትሌቲክሱ ድል የሚቀዳው ሃገራዊ ስሜት በእግር ኳሱም ቢሆን በተለያዩ አጋጣሚዎች\nሲንጸባረቅ ታዝበናል። እኤአ በ2013 የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በደቡብ አፍሪካ ዋንጫ ማለፏን ተከትሎ በህዝቡ ልብ ውስጥ የነበረው\nደስታ ከጥልቅ የሃገር ስሜት እንጂ ሌላ ምክንያት አልነበረውም። ዋልያዎቹ ከ31 ዓመት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ መሳተፍ የህዝቡ ብሄራዊ ስሜት እንዲገነፍል\nአድርጎት ታይታል። የኢትዮጵያዊነትን ስሜት ከገባበት ሰመመን በመቀስቀስ ህዝቡን ከዳር እስከ ዳር በአንድነት አስተሳስሯል፣ አስፈንጥዟልም።\nየልዩነት ነጋሪት ጉሰማውን ድምጽ በመዋጥ፤ የአንድነቱን ድምጸት አጉልቷል። ይህም በአትሌቲክስ ስፖርት የተገነባው ብሄራዊ ስሜትን\nዳግም እንዲያንሰራራ ያደረገ ትልቅ አጋጣሚ ከመሆን በተጓዳኝ ብሄራዊ መግባባት የፈጠረ ልዩ አጋጣሚ እንደነበርም ይታወሳል። ከትናንት በስቲያም ዋሊያው በቀጣዩ አመት ኳታር ለምታዘጋጀው የአለም ዋንጫ የቅድመ\nማጣሪያ ጨዋታውን ከሌሴቶ ጋር ሲያከናውን ከባህር ዳር ሰማይ ስር የሆነውም ይህን የታሪክ አጋጣሚ ዳግም ያስመለከተ ነበር። ብሄራዊ\nቡድኑን ለመደገፍ ከባህርዳርና አካባቢዋ የሚገኝ የሃገር ስሜት የኮረኮረው ደጋፊ ወደ ስታዲየም ማልዶ ነበር መትመም የጀመረው። ብሄራዊ ኩራቱን\nየተሸከሙለትን ዋልያዎቹን ለማበረታታት ከረፋዱ 5 ሰዓት ጀምሮ በህብረ ቀለማት ደምቆና ታጅቦ የተለያዩ ትዕይንቶች ያሳየበት ሁኔታም\nእጅጉን ደማቅ ነበር። አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀዩ ሰንደቅ በባህር ዳር ጎዳናዎች በድምቀትና በክብር ሲውለበለብ የነበረበት ሁናቴ ታሪክ\nራሱን የደገመበት ነበር። ሁለቱ ብሄራዊ ቡድኖች\nከሁለት አመት በፊት ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በባህር ዳር ስታዲየም ጨዋታቸውን ማካሄዳቸውና በዋልያዎቹ 2 ለ 1 አሸናፊነት መቋጨቱ\nየሚታወስ ሲሆን በወቅቱ በስታዲየም ከአፍ እስከ ገደፍ ሞልቶ በተጋጣሚው ቡድን ትልቅ የስነ ልቦና ችግር መፈጠር የቻለው ደጋፊ፣\nለዋልያዎቹ ተጨማሪ አቅምና ጉልበት ሆኖም ነበር። የትናንት በስቲያም\nፍልሚያ ምንም እንኳን በውጤት ሲቃኝ ታሪክ ራሱን ደግሞ ባይታይበትም፤ ደጋፊው ግን በጥልቅ የሃገር ፍቅር ብሄራዊ ኩራቱ የሆነውን\nብሄራዊ ቡድን ከማበረታታት አኳያ ታሪክን ደግሞ ሰርቶታል። ከማለዳ ጀምሮ በባህር ዳር ጎዳኖዎች የነበረው ከአገር ወዳድነት የሚፈለቀቀው\nጥልቅ ስሜትም፤ ጨዋታው ከተጀመረ በኋላ ይበልጥ ተጋግሎና ከፍ ብሎ ተሰምቷል። ሙሉ ዘጠና ደቂቃ\nበተለያዩ ህብረ ዝማሬዎች በማጀብ ብሄራዊ ኩራት ለሆኑት ዋልያዎቹ ብርታት ሲሆኑ ታዝበናል።”…ዋልያ… ዋልያ…” “…\nድሌ ማታ ነው ድሌ…” የደስታ ማጣጣሚያ ሆነው ሲሰሙ የነበሩ የባህር ዳር ስታዲየም ድምጾች ነበሩ። በእለቱ ከአፍ እስከ\nገደፍ በሞላው ስታዲየም የነበረው ትዕይንት በእርግጥም፤ ከባህር ዳር ሰማይ ስር በዋልያዎቹ ተመስሎ ብሄራዊ ኩራት በከፍታ ላይ ሲውለበለብ\nለመታዘብ ተችሏል። ምንም እንኳን በብሄራዊ ስሜት ብሄራዊ ቡድኑን ለማበረታታት የተሄደበት ርቀት ታሪክ ራሱን ቢደግምም በውጤት ደረጃ\nግን ራሱን መድገም የቻለ አልሆነም። በጨዋታ እንቅስቃሴ ብልጫ ማሳየት የቻሉት ዋልያዎቹ የሌሴቶን መረብ ለመድፈር ሳይችሉ ሙሉ ዘጠና\nደቂቃ ተጠናቋል። መከላከልን መሰረት ያደረጉት ሌሴቶዎች ግባቸው ሳይደፈር ነጥብ እንዲጋሩ አድርጓቸዋል። ከጨዋታው በኋላ የዋልያዎቹ አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ «ከምንግዜውም በተሻለ\nጥሩ ተጫውተናል፤ በርካታ የግብ እድሎችንም መፍጠር ችለናል፤ ነገር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎላ የመጣው የአጥቂ መስመር ክፍተት\nጎል ሳናስቆጥር እንድንወጣ አድርጎናል። በቀጣይ ጊዜ ግብ የማስቆጠር ችግራችን ለመቅረፍ በርትተን እንሰራለንም» ብለዋል። «90\nደቂቃ ያለእረፍት ከጎናችን በመሆን ያበረታንን ደጋፊ ከልብ ማመስገን እፈልጋለሁ።» ሲሉም በከፍተኛ ድጋፍ ለታጀቡት ዋልያዎቹ በተጋጣሚውን\nቡድን ላይ የጨዋታ የበላይነት እንዲያሳይ ሞራል እንደሆናቸው አስምረውበታል። የሁለቱ ብሄራዊ ቡድኖች የመልሱ ጨዋታም የፊታችን ጳጉሜን\n3 ቀን ቀጠሮ ተይዞለታል።አዲስ ዘመን ጳጉሜ 1/2011 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "482714e03c1dfdf36dd4124b3feb21e4" }, { "passage": "የተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከአስር ዓመት በፊት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመለክተው በተለያዩ ዓለምአቀፍ የስፖርት መድረኮች ስፖርተኞች በዘርና በቆዳ ቀለማቸው መገለል የተለመደ እንደሆነ ያትታል። ይህ እውነታ አሁን ላይ አደጉ በምንላቸው አገራት ስፖርት ላይ እንኳን ነቀርሳ መሆኑን በተለያዩ አጋጣሚዎች እንመለከታለን። በተለይም እንደ አሜሪካ፤ አውስትራሊያና አውሮፓ የመሳሰሉ አገራት ላይ ጥቁር ስፖርተኞች አሁንም ድረስ በዘረኝነት ሲዘለፉ፤ ሲንቋሸሹና ዝቅ ተደርገው የሚታዩባቸው አጋጣሚዎች እየተበራከቱ መምጣታቸው ከዘር፤ ከሃይማኖትና ከፖለቲካ ነፃ መሆን የሚገባው ስፖርት ላይ መጥፎ አሻራ እንዲያርፍ እያደረገ ይገኛል። በስፖርት ጥቁሮች አሁን ላይ በየትኛውም ዓለምአቀፍ መድረክ ተፎካካሪ እንዲሆኑ ከማስቻል\nባሻገር በትልቅ ደረጃ ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ለማሳየት በርካታ ጥቁር ከዋክብት ብዙ ችግሮችን ተጋፍጠዋል። በተለይም ጥቁር አሜሪካውያን\nአትሌቶች በዚህ ረገድ ያዩት ፈተና ሳይጠቀስ የሚታለፍ አይደለም። አፍሪካውያንም ቢሆኑ በርካታ መከራዎችን ተጋፍጠው ለታላቅ ክብር\nበመብቃት ለአሁኖቹ አትሌቶች ፋና ወጊ ሆነው እኩልነትን ማንፀባረቃቸው አይካድም። ለዚህም ታሪካዊውን ኢትዮጵያዊ የማራቶን ኮከብ\nአትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ በትልቁ የሚነሳ የጥቁር ህዝቦች ኩራት ሆኖ እናገኘዋለን። ኢትዮጵያውያን በስፖርቱ ብቻም ሳይሆን በዓደዋ\nድል የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌትና የመዓዘን ድንጋይ ሆነዋል። የጥቁር ህዝቦች ኩራት የሆነው የዓደዋ ድል የሚዘከርበት የካቲት\nወር በመላው ዓለምም የጥቁር ህዝቦች መታሰቢያ ሆኖ ይከበራል። በስፖርቱ ዓለም ለእኩልነት የታገሉ ቁንጮ አትሌቶችም በዚህ ወር ሳይዘከሩ\nአይታለፉም። በእርግጥ በስፖርት መድረክ ዘረኝነትን የታገሉ፤ እኩልነትን ያንፀባረቁና በድላቸው የጥቁር ህዝቦችን አንገት ያቀኑ በርካታ\nጥቁር ከዋክብቶች መኖራቸው አይካድም። ከእነዚህ ከዋክብቶች ግን ተፅዕኗቸው ከፍተኛ የነበረ፤ ድላቸው በርካታ ትርጉም የነበረውና\nበትልቅ ደረጃ የሚነሱትን ሦስት ጀግኖች ብቻ በዓድዋ ድል ዋዜማ ላይ ሆነን በስፖርት ማህደር አምዳችን እንመልከት። አበበ\nቢቂላ 1928 ፋሺስት ጣሊያን በአምባገነኑ ቤኒቶ ሞሶሎኒ ኢትዮጵያን ወረረ፤ ምስጋና ለማይዘነጉት\nጀግኖቹ አርበኞቻችን ይግባና ሞሶሎኒና ግብረአበሮቹ ብዙም ሳይደላደሉ ከአገር ቤት በቅሌት ተባረሩ። ከሃያ አራት ዓመታት በኋላ ታላቁ\nአበበ ቢቂላ ሮምን በባዶ እግሩ ወሮ ዓለምን ጉድ አሰኘ፤ የምን ጊዜም የማራቶን ንጉሡ የአፍሪካውያን ኩራትና የነፃነት ተምሳሌት\nእንዲሁም፤ የመጀመሪያው ጥቁር የማራቶን ኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ በጥቁሮቹ በጀግኖቹ መታሰቢያ ወር የካቲት የጥቁር ህዝቦች\nኩራት ሆኖ ከሃምሳ አምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመት ዋዜማ በሮም ኦሊምፒክ የፈፀመው ታሪካዊ ጀብድ በመላው ዓለም\nያሉ ጥቁር አትሌቶችን በእጅጉ ያኮራና ያነሳሳ ነበር። ጷግሜ 5ቀን 1952 አስራ ሰባተኛው የሮም ኦሊምፒያድ በታላቋ ሮም ጎዳናዎች\nአንድ ተዓምር ታየ፤ በርካቶች ዓይናቸውን ለማመን ተቸገሩ፤ በአንባገነኑ ሞሶሎኒ አገር በበርካታ ነጮች መሃል አንድ ጥቁር በባዶ\nእግሩ ታየ። የጥቁር ህዝቦች ተዓምርን ለመቀበል የሚተናነቃቸው ዘረኝነትን በደማቸው ያሰረፁ ነጮች እንዴት ይህ ሊሆን እንደቻለ ግራ\nተጋቡ። አፍሪካውያንን ያኮራ ኢትዮጵያውያንን ከልብ ያስፈነጠዘ ታሪካዊ ድል። የአራት ዓመት ታዳጊ ሆኖ እናት አገሩ ኢትዮጵያ በጣሊያን\nፋሺስት ስትወረር መጥፎውን ጊዜ ገና ባልጎለበተ የሕፃን አዕምሮው የሚያስታውሰው አበበ ቢቂላ ሃያ ስድስት ዓመታት ጠብቆ ታላቁን\nየሮም ጎዳና በባዶ እግሩ ወሮ የማይደገመውን ታሪክ ሠራ። ከአራት ዓመት በኋላም 1956 በድጋሜ ጫማ አጥልቆ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ክብረወሰን\nበማሻሻል ጭምር አሸንፎ ጥቁሮች በማይደፈረው ርቀት አሁን ላይ ቁንጮ እንዲሆኑ መሰረቱን አኖረ። እሱ በከፈተው በርም ቁጥር ስፍር\nየሌላቸው የማራቶን አትሌቶች ለዘመናት ርቀቱን የግላቸው አድርገው አሁን ድረስ ዘልቀዋል። ጄሴ ኦውንስ ታላቁ የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ እንደ 1936ቱ በዘረኝነት የተጨማለቀበትን ወቅት ማስታወስ ከባድ ነው። ገና ከጅምሩ\nአይሁዶችንና ጥቁሮችን ከኦሊምፒኩ ለማግለል እንዲሁም የነጮችን የበላይነት አስተሳሰብ የመደገፍ አባዜ የተጠናወተው ዘረኛው የናዚ\nመሪ አዶልፍ ሂትለር ውድድሩ በአገሩ ጀርመን እንደሚካሄድ ካወቀ አንስቶ ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም። ይህ ኦሊምፒክ ብዙ ተቃውሞ\nቢገጥመውም ከውድድሩ ራሳቸውን ያገለሉና እንዳይሳተፉ የተደረጉ አይሁዳውያን ነበሩ። በውድድሩ የተሳተፉትም ቢሆኑ በሂትለር ትዕዛዝ\nየተገለለ የመለማመጃ ሜዳና የውድድር ቁሳቁስ እንዲጠቀሙ ተደርገዋል። ጥቁሮችም በዚህ ኦሊምፒክ ተመሳሳይ ዕጣ ፋንታ የገጠማቸው ሲሆን\nየበታች እንደሆኑ ለማሳየት ያልተደረገ ጥረት አልነበረም። ይህን ጥረት ሁሉ ውድቅ አድርጎ የሂትለርን ቆሽት ያሳረረ አንድ ክስተት\nግን በጥቁሩ አሜሪካዊ አትሌት ጄሴ ኦውንስ ተፈፀመ። ኦውንስ በዚህ የበርሊን ኦሊምፒክ በመቶ፤ በሁለት መቶ፤ በረጅም ዝላይና አራት\nበመቶ የዱላ ቅብብል ውድድሮች አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ጠራርጎ በመውሰድ ጥቁሮች አንገታቸውን ያቀኑበት ነጮች ደግሞ የተሸማቀቁበትና\nለመቀበል ያቃራቸውን ድል አጣጣመ። ይህ አልዋጥለት ያለው ሂትለር ግን በሽልማት ስነ ስርዓቱ ላይ ኦውንስን ላለመጨበጥና ለድሉም\nእውቅና ላለመሰጠት ራሱን አሳምኖ ስቴድየሙን በድንፋታ ለቆ ወጣ። የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ፍራንክሊን ሩዝቬልትም ቢሆኑ ለኦውንስ\nድል እውቅና ሳይሰጡት ቀርተዋል። ኦውንስ ይህ ገድሉ በዘረኛ ነጮች እውቅና ይነፈገው እንጂ ነጮች ወደዱም ጠሉም ከጥቁሮች እኩል\nእንደሆኑ ልቦናቸው እንዲያምን አስገድዷቸዋል። በአንድ አገር ውድድሮች የነጭና የጥቁር ተብሎ ተከፍሎ በሚካሄድባት አሜሪካም በወቅቱ\nየኦውንስ ድል ትልቅ ትርጉም ነበረው። በዚህም ኋላ ላይ እኤአ 1976 የአሜሪካውያን ትልቁ ሽልማት የሆነውን የነፃነት ሜዳሊያ ሊሸለም\nበቅቷል። ኦውንስ ህይወቱን በሙሉም የጥቁሮች መብት እንዲከበር ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ጥብቅና ከመቆም ባሻገር የእሱን ፋና ተክለው\nለመጡ ጥቁር አትሌቶች ሁሉ ትልቅ የመንፈስ ብርታት በመሆን ከጎናቸው ሲቆምና ሲሟገት ኖሯል። መሐመድ አሊየምን ጊዜም የቦክስ ስፖርት ንጉሡ መሐመድ አሊ የዓለም የቦክስ ቻምፒዮንና ታላቅ የቡጢ ተፋላሚ ብቻ አልነበረም። የሰብዓዊ\nመብት ተሟጋች፤ የጥቁር ህዝቦች ሰንደቅ፤ በመላው ዓለም በስፖርትና በታላቅ ስብዕና ተምሳሌትም ጭምር ነው። ብዙዎች ቦክስ ስፖርት\nሳይሆን የጥጋበኞች ድብድብ አድርገው ከመሳል አስተሳሰብ አውጥቶ የቦክስን ስፖርት ጥበባዊ ገፅታ በማላበስ ተወዳጅና አሁን ላይ በዓለማችን\nበአንድ ጊዜ በርካታ ሚሊየን ዶላሮች የሚያሳቅፍ ግንባር ቀደም ስፖርት እንዲሆን ተፅዕኖውን አሳርፏል። መሐመድ የትውልድ ስሙ ካሴስ\nክሌይ ቢሆንም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ባሮችን ነፃ ለማውጣት በታገሉ ታላቅ ሰው መታሰቢያነት የወጣለት ስም ነበር፡፡ ለመጀመርያ ጊዜ\nየዓለም ከባድ ሚዛን ቻምፒዮን ከሆነ በኋላ በማግስቱ ስሙን ለመቀየር ወሰነ፡፡ የነፃነት ታጋዩን ማልኮለም ኤክስ ከጎኑ አድርጎ በሰጠው\nመግለጫ «ዘ ኔሽን ኦፍ ኢስላም» የተባለውን ተቋም መቀላቀሉን በማሳወቅ የባርያ ስም ይለው የነበረውን ካሴስ ክሌይ በመቀየር በቀድሞ\nስሙ ላለመጠራት ወሰነ። በወቅቱ «ኔሽን ኦፍ ኢስላምን» ይመራ የነበረው ኤልጅያህ መሃመድ እኤአ በ1964 ላይ መሐመድ አሊ የሚለውን\nስም ካወጣለት በኋላ እሱን በማፅደቅ እስከ ህይወት ዘመኑ መጨረሻ ተጠራበት። ታሪካዊው ኢትዮጵያዊ አትሌት አበበ ቢቂላ በ196o\nየሮም ኦሊምፒክ በባዶ እግሩ ሮጦ ለጥቁር ህዝቦች የመጀመሪያውን የማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ሲያስመዘግብ መሐመድ አሊም በቦክስ የወርቅ\nሜዳሊያ አጥልቆ ነበር። ሁለቱ ታሪካዊ የጥቁር ህዝቦች ከዋክብት ፊርማቸውን ተለዋውጠውም ነበር። ይሁንና መሐመድ አሊ ይህን የወርቅ\nሜዳሊያውን ለአገሩ ከማበርከት ይልቅ በሊውስ ቪል ግዛት በሚገኘው የኦሃዮ ወንዝ ጨምሮታል። ሜዳሊያውን ለአሜሪካና ለትውልድ ከተማው\nሊውስ ቪል ቢቀዳጅም በርገር የመግዛት መብት ባለመኖሩ ተቃውሞውን ለመግለፅ ነበር ይህን ርምጃ የወሰደው። በ1996 አገሩ አሜሪካ\nባስተናገደችው የአትላንታ ኦሊምፒክ ችቦውን እንዲለኩስ ከመደረጉ ባሻገር ወንዝ የጨመረው የወርቅ ሜዳሊያ ምትክ ሌላ ሜዳሊያ በአንገቱ\nተጠልቆለታል። በ1970 የዶክተር ማርቲን ሉተር ኪንግ መታሰቢያ ሽልማት የተቀበለው መሐመድ አሊ፤ የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነት ተምሳሌት\nሆኖም ያውቃል። የተባበሩት መንግሥታት የሰላም መልዕክተኛ ሆኖም ከ1998 እሰከ 2008 በታዳጊ አገራት በመዘዋወር አገልግሏል።\nታላቁን የደቡብ አፍሪካ ነፃነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ከእስር እንደተፈቱ በአካል ተገኝቶ ደስታውን ለመግለፅ መሐመድን የቀደመው\nአልነበረም። አዲስ ዘመን የካቲት 22/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "a13d4682ea6c8101e24c752970fd973f" } ]
f60e2e4b225d6b2b43a1c308e0d4c2c2
62db70ce50bc06bee8fd179408ba0e6e
የሴቶችን የማራቶን ታሪክ የቀየረችው ታሪካዊ ቅፅበት
 የታሪክ ድርሳናት እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ የዓለም ስፖርት ካንቀላፋበት ፆታን እኩል ያለመመልከት ቅዠት እንዳልነቃ ይመሰክራሉ። ባልተሞከረና ባልተረጋገጠ ሁኔታ ‹‹አትችልም›› የሚል መላ ምት ሚዛን ደፍቶ ዘመናትን በመሻገሩ እጅግ ተወዳጁና ተመራጩ የመዝናኛ ዘርፍ ወደ አንድ ጎን ያዘነበለ ነበር። ሴት በስፖርት ትጥቅ ከሜዳ መገኘቷን ባለመቀበል አስተሳሰብ የተሸበቡትን ለማሳመንም በርካቶች ባልተፈቀደ መንገድ መገኘት ግድ ሆኖባቸዋል። ‹‹ነውር›› ለሚሏቸው ጆሯቸውን ሳይሆን ጀርባቸውን በሰጡ ደፋርና ቆራጥ ሴቶች መቻላቸውን በማስመስከር ዓለም የዛሬውን ቅርጽ እንዲይዝ አድርገዋል። የዛሬውን የሴቶች ቀን አስመልክቶም ‹‹ባልተፈቀደው›› መንገድ ከተጓዙ እንስቶች መካከል የአንዲትን ሴት ታሪክ ልናስታውስ ወደድን። በዓለም ላይ ዋና ዋና ከሚባሉት ስድስት ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች መካከል አንዱ የቦስተን ማራቶን ነው። መነሻውን እኤአ 1897 ያደረገው አንጋፋው የጎዳና ላይ ሩጫ የ122 ዓመት እድሜ ባለጸጋም ነው። ታዲያ በዚህ ውድድር ተሳታፊ እንዲሆኑ ይፈቀድላቸው የነበሩት ወንድ አትሌቶች ብቻ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የሴቶች ተሳትፎ የሚጀምረው ዘግየት ብሎ ነው። በዓለም አትሌቲክስ ታላቅ ስፍራ ያለው ይህ ማራቶን የተለያዩ ክስተቶችን በተለያዩ ዓመታት ቢያስተናግድም ከሁሉም ይልቅ ሴቶች በሩጫው ላይ እንዲታዩ መሰረት የጣለው ድራማዊ ክስተት መቼም የሚዘነጋ አይደለም። እኤአ 1967 የቦስተን ማራቶን ተሳታፊ ለመሆን ከተመዘገቡት ወንድ ሯጮች መካከል ኬቪ ስዊዘር የሚል ስም ይገኝበታል። ስሙ በአጭሩ የተመዘገበ በመሆኑ ጾታው በትክክል የሚለይ ባይሆንም ለሩጫው ፈቃድ የሚያገኙት ወንዶች ብቻ በመሆናቸው ይህ ይከሰታል በሚል የጠረጠረ አልነበረም። የውድድሩ ዕለት ደርሶ የሩጫ ማስጀመሪያው ከተበሰረ በኃላ ግን ሯጮች ያዩትን ማመን አልቻሉም። ምክንያቱ ደግሞ በከባዱ የማራቶን ሩጫ ከእነዚያ ሁሉ ወንዶች መካከል አንዲት ሴት በመታየቷ ነው። ከቆይታ በኋላ ግን ክስተቱ ከሯጮችም አልፎ ከመንገዱ ዳር ቆመው ከሚያበረታቱና ለዘገባ በተሰየሙ የመገናኛ ብዙሃን እይታ ውስጥ ይገባል። ጉዳዩ ያስደነቃቸው የፎቶግራፍ ባለሙያዎችም ሩጫውን እየተከተሉ ካሜራቸውን ወደዚያው መደቀናቸውን ተያያዙት። ይህ ትዕይንት በዚህ ሁኔታ እንዳለ ግን በጎዳናው ግራና ቀኝ ካሉት ተመልካቾች መካከል ባልተለመደ መልኩ አንድ ሰው ሩጫውን ተቀላቀለ። የውድድሩን ክልል ጥሰው የገቡት አንጋፋ ሰውም እሳት ለብሰውና እሳት ጎርሰው ከሴቷ ሯጭ ጋር ግብግብ ጀመሩ፤ ነገር ግን ገላጋዮች በመሃል በመግባታቸው ከጀመረችው ሩጫ ሊገቷት አልቻሉም።ዕድሜ ሰጥቷት ዛሬን ለመመልከት የበቃችው የዚህ ታሪክ ባለቤት ካትሪን ስዊዘር ትባላለች። በጊዜው የሆነውን ስትተርክም ‹‹በረጅም ርቀት ሩጫዎች ላይ ሴቶች ለምን አይሳተፉም የሚለው የሁልጊዜም ጥያቄዬ ነበር። በሩጫው ላይ ለመሳተፍ ስነሳም እንዳይለዩኝ በሚል ስሜን አሳጥሬ ኬቪ ስዊዘር አደረኩት፤ በውድድሩ ዕለትም ከአሰልጣኜና የእግር ኳስ ተጫዋች ከሆነው ፍቅረኛዬ ጋር ተገኘሁ። ሩጫውን እንደጀመርንም ብዙዎች ሴት መሆኔን በመመልከት ተደንቀው ሲያዩኝ ‹‹አዎ እኔ ሴት ነኝ›› እላቸው ነበር፤ የካሜራ ባለሙያዎችም ፎቶ ሊያነሱኝ ሲከተሉኝ እንደነበር አስታውሳለሁ። ከቆይታ በኋላ ግን የውድድሩ ዳይሬክተር በንዴት ወደእኔ መጣ፤ የመሮጫ ቁጥሩን ስጪኝና ከዚህ ውድድር ውጪ እያለ ይጮህና ይጎትተኝም ነበር። በፊቱ ላይ ይታይ የነበረው ብስጭት የሚያስፈራ ቢሆንም አብሮኝ የነበረው ፍቅረኛዬ በመሃላችን በመግባት እኔን ወደፊት እንድሄድ ነገረኝ። አንዳንድ ሯጮች ግን ከኋላዬ እስኪቀሩ ድረስ ‘መቻልሽን ለማስመስከር ነው ምትሮጪው፣…?’ በማለት ሲያሾፉብኝ ነበር›› ትላለች በተንቀሳቃሽ ምስል የታገዘውን የዚያኔውን ሁኔታ ስታስታውስ።ካትሪን ከዚያ በኋላ የነበሩትን ኪሎ ሜትሮች የሸፈነቻቸው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ነበር። ፍቅረኛዋ ሩጫውን ስለማጠናቀቅ በጠየቃት ጊዜም ‹‹በእጄና ጉልበቴ ድኼም ቢሆን እጨርሰዋለሁ አልኩት፤ ምክንያቱም ሩጫውን ካላጠናቀቅኩ ማንም የሴትን መቻል አይረዳም እያልኩ አስብ ነበር። እጨርሰዋለሁ እንዳልኩትም በ 4ሰዓት ከ20 ደቂቃ የመጨረሻውን መስመር ረገጥኩ፤ ምሽት ላይ ወደ ቤታችን ስንመለስም ክስተቱ ህይወቴን እንደቀየረው ተገነዘብኩ። ምክንያቱም በመንገዳችን ላይ ቡና ለመጠጣት ካረፍንበት ስፍራ ፎቶዬን የያዙና እኔን ዜና ያደረጉ በርካታ ጋዜጦችን በመመልከቴ ነው። በመጨረሻም ያደረኩት ነገር ሴቶች በስፖርት ያላቸውን ታሪክ ይቀይር ይሆናል በሚል ተስፋ አሳደረብኝ›› ትላለች ጠንካራዋ ካትሪን ስዊዘር። የ73 ዓመቷ ካትሪን ዛሬ ደራሲና የቴሌቪዥን አስተዋዋቂ ሆናለች። እርሷ የጀመረችው በቦስተን ማራቶን የሴቶች ተሳትፎም ከአምስት ዓመት በኋላ እኤአ በ1972 እውን ሲሆን፤ እኤአ በ1975 ለሁለተኛ ጊዜ ተሳትፋ የራሷን ምርጥ ሰዓት (2:51:37) በማስመዝገብ አሸናፊ ሆናበታለች። አሁን ዓመታዊው የቦስተን ማራቶን ሲካሄድ በክብር እንግድነት ትገኛለች፤ ሌሎች ሴቶች ሲመለከቷትም ለቅሶ እንደሚቀድማቸው ትናገራለች። የመጀመሪያ ሩጫዋን ባደረገችበት ዓመት የመሰረተችው የሴቶች ማህበርም እስከሁንም በአሜሪካ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። አዲስ ዘመን የካቲት 29 /2012  ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28730
[ { "passage": "በ2019 የአትሌቲክሱ ዓለም የውድድር ዓመቱ ገና ሳይጠናቀቅ በአስደናቂ ‹‹የይቻላል›› መንፈስ የደመቀበት እንደሆነ ሁሉ ከምን ጊዜውም በላይ ጥያቄዎች የተነሱበት ዘመን ሆኗል፡ በተለይም ባለፉት ሁለት ሳምንታት የአትሌቲክሱ ዓለም አበይት ክስተቶችን ማስተናገዱን ተከትሎ በርካታ የመገናኛ ብዙሃን በስፖርቱ ዓለም ሰፊ ሽፋን ሰጥተው የሚያራግቡት ጉዳይ አግኝተዋል፣ የማህበራዊ መገናኛ ብዙሃንም ቢሆኑ በአትሌቲክስ ጉዳዮች የተጨናነቁበት ወቅት ነበር፡፡ ገና ከጥንስሱ ብዙ ውዝግቦች የተከተሉት የዶሃው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና፣ የሰው ልጅ ማራቶንን ከ2ሰዓት በታች ሮጦ ማጠናቀቅ እንደሚችል የታየበት አጋጣሚ፣ የሴቶች የዓለም የማራቶን ክብረወሰን ከአሥራ ስድስት ዓመታት በኋላ ሳይታሰብ የተበሰረበት፣ እውቁና ስኬታማ አትሌቶችን ማፍራት የቻለው የረጅም ርቀት አሰልጣኝ አልቤርቶ ሳላዛር ከአበረታች መድሃኒት ጋር በተያያዘ ለአራት ዓመታት ከስፖርቱ የታገዱበት አበይት ክስተቶች ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ነበር የተከናወኑት፡፡ እነዚህ ክስተቶች በአትሌቲክሱ ዓለም አስደናቂ ብቻ ሆነው አላለፉም፡፡ በርካታ ጥያቄዎችን በስፖርቱ ዙሪያ በርትተው እንዲነሱም አድርገዋል፡፡ ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች\nየመሮጥ ስኬት ኬንያዊው አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ ከሳምንት በፊት ማራቶንን ከ2ሰዓት በታች ሮጦ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ቬና ላይ አሳይቷል፡፡ ይህም በስፖርቱ ትልቅ መነቃቃትን ከመፍጠር ባሻገር የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ግንዛቤ ፈጥሯል፡፡ ኪፕቾጌ ይህን ማሳካት የቻለው ከመነሻው ከውዝግብ በፀዳ መልኩ አልነበረም። ይህን ስኬት በርካቶች ከስፖርታዊ ኩነቱ ነጥለው በመመልከት አትሌቱ ተጫምቶት የሮጠበትን የናይኪ ጫማ የማስተዋወቅ የንግድ ሥራ አድርገው ተመልክተውታል፡፡ በንግዱ ዓለም ፍልስፍና ብዙ የሚዋጥ ባይሆንም ናይኪ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ በመላው ዓለም ትልቅ ስም እያለው በዚህ መንገድ ስፖርቱን ተጠቅሞ ምርቱን ለማስተዋወቅ መሞከሩ ሌሎች ተፎካካሪዎቹን ለመዋጥ ያደረገው ስግብግብነት እንደሆነ ያስቀመጡ ወገኖችም ጥቂት አይደሉም፡፡ የሰው ልጅ በተፈጥሯዊ መንገድ ሮጦ ማራቶንን ከ2ሰዓት በታች ማጠናቀቅ እየቻለ ኪፕቾጌ በምቹ የውድድር ቦታ ላይ በረቀቀ ቴክኖሎጂ ታግዞ ማሳካቱ ከስፖርት መርህ ጋር ተቃራኒ እንደሆነ የሚያነሱም አሉ፡፡ በአርቴፊሽያል ነገሮች በአትሌቲክሱ መግባት ከጀመሩ ወደ ፊት ስፖርቱ አሁን ያለውን የፉክክር ለዛ ይዞ አይቀጥልም የሚል ስጋት ያላቸው የስፖርት ቤተሰቦች ከዚህም ከዚያም አትሌቲክሱ ላይ ጠንካራ ጥያቄና ትችት ሲሰነዝሩ ሰንብተዋል፡፡ የሴቶች የማራቶን ክብረወሰን\nኪፕቾጌ ቬና ላይ በአርባ አንድ አሯሯጮች ታግዞ አርባ ሁለት ኪሎ ሜትርን 1፡59፡40 ካጠናቀቀ ከሃያ አራት ሰዓት በኋላ በቺካጎ ማራቶን ኬንያዊቷ ብሪግድ ኮስጌ ማንም ያልጠበቀውን የዓለም ክብረወሰን ማሻሻል ችላለች፡፡ ኮስጌ በእንግሊዛዊቷ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ለአሥራ ስድስት ዓመታት ተይዞ የቆየውን 2፡15፡25 ክብረወሰን በሰማንያ አንድ ሰከንድ አሻሽላለች፡፡ ራድክሊፍ ለአሥራ ሰባት ዓመት በስሟ የቆየው የዓለም ክብረወሰን ከእጇ መውጣቱ በርካታ የምዕራቡ ዓለም መገናኛ ብዙሃንን ያስደሰተ አይመስልም፡፡ ቤልፋስት ቴልግራምን ጨምሮ በርካታ ድህረ ገፆች የኬንያዊቷ አትሌት አዲስ ክብረወሰን ላይ ጥያቄ ማንሳታቸው አልቀረም፡፡ ይህም የአትሌቷ ወኪል ፌደሪኮ ሮሳ ከዚህ ቀደም አብሯቸው የሚሰሩ በርካታ አትሌቶች የአበረታች መድኃኒት ተጠቃሚ ሆነው መገኘት ነው፡፡ ከዚህ ወኪል ጋር የሰሩት በርካታ ኬንያውያን አትሌቶች፣ የቀድሞው የ1500 ሜትር ቻምፒዮን አስቤል ኪፕሮፕ፣የ2016 የለንደን ማራቶን ቻምፒዮን ጀሚማ ሱምጎንግ፣\n2013 ላይ የቺካጎ ማራቶንን ያሸነፈችው ሪታ ጂፕቶ(በኋላ ላይ አሸናፊነቷ ተሰርዞ ለኢትዮጵያዊቷ ማሬ ዲባባ ተሰጥቷል) አበረታች መድኃኒት ተጠቃሚ ሆነው መገኘታቸው ይታወቃል፡፡ ያም ሆኖ አዲስ ክብረወሰን ያሻሻለችው አትሌት ለጊዜው የተገኘባት ጥፋት የለም፡፡ ይህች አትሌት አበረታች መድኃኒት ተጠቅማ ባትገኝ እንኳን የተጫማችው መሮጫ ጫማ ፓውላ ራድክሊፍ ክብረወሰን ስትሰብር ከተጫማችው ከ60 እስከ 90 ሰከንድ አትሌቷን የማፍጠን ጥቅም ስላለው ያሻሻለችውን 81 ሰከንድን እውቅና ላለመስጠት ጥረት ሲያደርጉ ታይተዋል፡፡ የአልቤርቶ ሳላዛርና የአትሌቶቹ\nጉዳይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆነው የአትሌቲክስ ረጅም ርቀት አሰልጣኝ አልቤርቶ ሳላዛር የተከለከሉ አበረታች ቅመሞችን ከቦታ ቦታ ማዘዋወርን (Trafficking) ጨምሮ የፀረ- ዶፒንግ እንቅስቃሴውን በማወክ (Tampering) እና በተለያዩ የፀረ-ዶፒንግ የህግ ጥሰቶች ተጠርጥሮ ጉዳዩ በአሜሪካ የፀረ- ዶፒንግ ኤጀንሲ (USADA) ሲጣራ ቆይቷል። በዚህም መሠረት ግለሰቡ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ለአራት ዓመታት በስፖርቱ ውስጥ እንዳይሳተፍ እገዳ የተጣለበት ከሁለት ሳምንት በፊት ነበር፡፡ የአሰልጣኙን እገዳ ተከትሎ በኦሊምፒክና በዓለም ቻምፒዮና እጅግ ስኬታማ የሆኑ አትሌቶቹ ከጥያቄ ሊያመልጡ አልቻሉም፡፡ እነዚህ አትሌቶች ላይ ግን ጠንከር ያለ ምርመራና አንዳችም እገዳ አለመጣሉ በበርካቶች ነገሩን ይበልጥ በጥርጣሬ እንዲመለከቱት አድርጓል፡፡ ከነዚህ አትሌቶች መካከል በ5ና 10 ሺ ሜትር ውድድሮች በሁለት ኦሊምፒክና ሦስት የዓለም ቻምፒዮናዎች መንገስ የቻለው ትውልደ ሶማሊያዊ የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ ይገኝበታል፡፡ ፋራህም ይሁን ሌሎች በሳላዛር ስር ሲሰለጥኑ የነበሩና ያሉ አትሌቶች ስለ አሰልጣኙ ሲነሳባቸው ምቾት አይሰማቸውም። ተመሳሳይ ጥያቄ ከጋዜጠኞች ሲነሳባቸውም በንዴት ከመመለስ አልፈው ለፀብ የሚጋበዙበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም። ፋራህም ከሳምንት በፊት በቺካጎ ማራቶን ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ይህ ነገር ገጥሞታል፡፡ ራሳቸው የእንግሊዝ መገናኛ ብዙሃንም ፋራህ በቺካጎ ማራቶን ስምንተኛ ሆኖ ከማጠናቀቁ ባሻገር በማራቶን ሕይወቱ ዝግተኛውን ሰዓት ማስመዝገቡ ከአሰልጣኙ ጋር በተያያዘ በተነሳው ውዝግብ ሳይረበሽ እንዳልቀረ ሲዘግቡ ሰንብተዋል፡፡ በተመሳሳይ በሳላዛር አሰልጣኝነት የኦሊምፒክ የ10ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያና በዓለም ቻምፒዮና የማራቶን ነሐስ ሜዳሊያ ያጠለቀው አሜሪካዊው አትሌት ጋለን ሩፕና ጆርዳን ሃሰይ ቺካጎ ማራቶን ላይ ማጠናቀቅ አለመቻላቸው በጤና እንዳልሆነ ብዙዎቹ ምክንያታዊ ሆነው ሲከራከሩ ተሰምተዋል፡፡ አሰልጣኝ ሳላዛር የሚመራው የናይኪ ኦሪገን አትሌቲክስ ፕሮጀክት የአሰልጣኙን እገዳ ተከትሎ ትጥቅ አምራች ኩባንያው ስሙ እንዳይጠለሽ በማሰብ ከቺካጎው ማራቶን ሦስት ቀናት በፊት ተዘግቷል፡፡ የፕሮጀክቱ ሰልጣኞች የሆኑት ሁለቱ አሜሪካውያን አትሌቶች ጋለን ሩፕና ጆርዳን ሃሰይም አዲስ የስልጠና መንገድ እያፈላለጉ መሆኑ ተነግሯል፡፡ አወዛጋቢው የዶሃ የዓለም\nቻምፒዮና ከሰባት ዓመት በፊት 17ኛው የዓለም ቻምፒዮና በመካከለኛው ምስራቅ የነዳጅ አገር ኳታር ዶሃ እንዲዘጋጅ ውሳኔ ላይ መደረሱን ተከትሎ በርካታ ጥያቄዎች ሲነሱ ነበር፡፡ ከፍተኛ የሙቀትና የወበቅ መጠን የበርቴዋን አገር ድግስ ያደፈርሳል የሚል ስጋት ከየአቅጣጫው መነሳቱ አንድ ፈተና ነበር፡፡ ምዕራባውያን ከጅምሩም የሰብዓዊ መብት ረገጣ ባለባት አገር ቻምፒዮናው መደረጉ ሲተናነቃቸው ታይቷል። ተዋጠላቸውም አልተዋጠላቸውም መካሄዱ ግን አልቀረም፡፡ ዶሃ ገንዘቤን ይጭነቀው ብላ ታሪካዊው የከሊፋ ዓለም አቀፍ ስቴድየሟን እጅግ በዘመነ ቴክኖሎጂ አስውባ ከጅምሩ እንቅፋት ይሆናል ተብሎ ለተሰጋው የሙቀት መጠን ማቀዝቀዣ በመግጠም ጥያቄውን መልሳለች፡፡ ያምሆኖ ተፈጥሮን ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥሯ ስር ማዋል አትችልምና ከስቴድየም ውጪ የተካሄዱ ውድድሮች ላይ እንከን መፈጠሩ አልቀረም፡፡ በሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያውያኑን ሦስት አትሌቶች ጨምሮ ከ68 አትሌቶች 28ቱ አቋርጠው መውጣታቸውን ተከትሎ እንከን ለማውጣት ለሚታትሩት የምዕራባውያን መገናኛ ብዙሃኖች ‹‹ድሮም ተናግረን ነበር›› እንዲሉ አድርጓል፡፡ የስታድየም ወንበሮች በተመልካች ድርቅ መመታታቸውም ሌላ አሉታዊ ክስተት መሆኑ አልቀረም፡፡ ያም ሆኖ ከቻምፒዮናው መጠናቀቅ በኋላ የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ የዶሃ ቻምፒዮና ከዚህ ቀደም ከተካሄዱት ሁሉ ቁጥር አንድ መሆኑን መናገራቸው ጥያቄ አስነስቷል፡፡ የአሰልጣኝ ሳላዛር ጉዳይ በዶሃው የዓለም ቻምፒዮናም ጥቁር ጥላ ማጥላቱ አልቀረም፡፡ በተለይም ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን በ1500ና በ10ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያ ማጥለቋ የአሰልጣኝ ሳላዛር ፍሬ እንደመሆኗ የስፖርት ቤተሰቡ ጥያቄ ቢያነሳ አያስገርምም፡፡ ናይኪና የእንግሊዝ አትሌቲክስ\nባለስልጣናት ግዙፉ ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ አሰልጣኝ ሳላዛር ከታገደ ወዲህ በኦሪገን የሚገኘውን የአትሌቲክስ ፕሮጀክት ቢዘጋም ከስፖርቱ ጋር ያለው ሰፊ ቁርኝት አሁንም በጥርጣሬ አይን ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ የአሰልጣኝ ሳላዛር ጉዳይ ከራሱና ከአትሌቶቹ ባሻገር ይዞ የሚመጣው በርካታ መዘዝ እንዳለም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወጣ ይገኛል፡፡ የእንግሊዝ አትሌቲክስ የአትሌቶች ብቃት ዳይሬክተር ኔል ብላክ በቺካጎ ማራቶን ሞ ፋራህን ለመርዳት በተገኘበት ወቅት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡ ከብላክ በተጨማሪም ከሳላዛር ጋር ተያይዞ በርካታ የእንግሊዝ አትሌቲክስ ባለስልጣናት ምርመራ ሊደረግባቸው ይገባል የሚሉ ግፊቶች በርትተዋል፡፡ምክንያቱ ደግሞ አሰልጣኝ ሳላዛር ለበርካታ ዓመታት የእንግሊዛውያን ረጅም ርቀት አትሌቶች አማካሪ ሆኖ ማገልገሉ ነው፡፡ ታላላቅ አትሌቶችንና ውድድሮችን ስፖንሰር በማድረግ አትሌቲክስ የገባበት ሁሉ የሚገባው ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ አትሌቶች አበረታች መድኃኒት አውቀውም ይሁን ሳያውቁ እንዲጠቀሙ በማድረግ ይታማል፡፡ በርካታ በአበረታች መድኃኒት ተጠቃሚነት የተቀጡና የሚጠረጠሩ አትሌቶችም ከዚህ ትጥቅ አምራች ጋር ግንኙነት ያላቸው ሆነው መገኘቱም ናይኪ ላይ ያለውን ጥርጣሬ ሚዛን እንዲደፋ አድርጎታል። ታዲያ አትሌቲክሱ ከዚህ ኩባንያ ጋር ያለውን ግንኙነት መለስ ብሎ መቃኘት አለበት የሚሉ የስፖርት ቤተሰቦች ጥርጣሬያቸው ጠንካራና ምክንያታዊ መነሻ የለውም ማለት እንዴት ይቻላል? አዲስ ዘመን ጥቅምት 10/2012ቦጋለ አበበ ", "passage_id": "a4207428d40f85ba8a4fd50d6e588bcf" }, { "passage": "ያለፈው ሳምንት በአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ ታላላቅ ውድድሮች የተስተናገዱበት ሆኖ አልፏል። ከቤት ውስጥ በርካታ ውድድሮች አንስቶ እስከተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮችም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በድል ተንቆጥቁጠው ታይተዋል። ከጣፋጭ ድሎቻቸው ባሻገርም በተለያዩ ርቀቶች ፈጣን ሰዓቶችና ክብረወሰኖች ማስመዝገብ ችለዋል። ትናንት ማለዳ በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ በተካሄደው የራስ አል ኪማህ ግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን ያስመዘገቡት ውጤት በጉልህ የሚጠቀስ ሲሆን በሁለቱም ፆታ ፈጣን ሰዓቶች ተመዝግቦበታል። በሴቶች መካከል በተካሄደው ውድድር ሰንበሬ ተፈሪ በርቀቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳትፋ 1፡05፡45 በሆነ ሰዓት አሸናፊ ሆናለች። ይህም በታሪክ በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎ የተመዘገበ ፈጣን ሰዓት ሲሆን የኢትዮጵያ ክብረወሰን ሆኖ ሊመዘገብም ችሏል። እጅግ ጠንካራ ፉክክር በታየበት ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ አራት ባለው ደረጃ ውስጥ ሲያጠናቅቁ የዓለም ግማሽ ማራቶን የክብረወሰን ባለቤት የሆነችው ነፃነት ጉደታ እስከ መጨረሻ ድረስ ታግላ ለጥቂት በመቀደሟ በተመሳሳይ ሰዓት ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ዘይነባ ይመር 1:05:46 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ሆና ስትፈፅም ደጊቱ አዝመራው በ1:06:07 ሰዓት ተከታዩን ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በዚህ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች እስከ መጨረሻ ያደረጉት አጓጊ ፉክክር ከአንድ እስከ ሦስት ባለው ደረጃ ያጠናቀቁ አትሌቶች የገቡበት ሰዓት ልዩነት የአንድ ሰከንድ ብቻ እንዲሆን አድርጎታል። በተመሳሳይ በወንዶች መካከል በተካሄደው ውድድር ለድል ሲጠበቁ የነበሩ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ቀዳሚውን ደረጃ በኬንያዊው ስቲፈን ኪፕሮፕ ቢነጠቁም ሁለተኛና ሦስተኛ ሆነው አጠናቀዋል። የአሸናፊነት ግምት ተሰጥቶት የነበረው አባዲ ሃዲስ ድንቅ ፉክክር ቢያሳይም በአጨራረስ ድክመት ኪፕሮፕ በሁለት ሰከንድ 58፡42 በሆነ ሰዓት ቀዳሚ መሆን ችሏል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ፍቃዱ ሃፍቱ 59:08 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ሆኖ ውድድሩን ጨርሷል። ኪፕሮፕ ያስመዘገበው ሰዓት የውድድሩ ክብረወሰን ከነበረው ሰዓት ጋር እኩል ሲሆን በርቀቱም በታሪክ አምስተኛው ፈጣን ሰዓት መሆን ችሏል። ካለፈው ረቡዕ አንስቶ በተለያዩ የዓለማችን ከተሞች ሲካሄድ በነበረው የቤት ውስጥ የዙር ውድድርም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አስደናቂ ውጤት አስመዝግበዋል። ፖላንድ ቶሩን በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮኑ ወጣት አትሌት ሳሙዔል ተፈራ የውድድር ዓመቱን መሪ ሰዓት3:35.57 በማስመዝገብ አሸናፊ ሆኗል። በዚህ ውድድር ልምድ ያለው ኢትዮጵያዊ አትሌት አማን ወጤ እልህ አስጨራሽ ፉክክር ቢያደርግም በመጨረሻዎቹ ሦስት መቶ ሜትሮች የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ሳሙዔል ተፈራ እጅ የሚሰጥ አልነበረም። በተመሳሳይ ቀንና ቦታ በሴቶች ስምንት መቶ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሃብታም አለሙ በፈጣን ሰዓት ታጅባ ያሸነፈችበት ክስተትም ያልተጠበቀ ነበር። አትሌት ሃብታም አለሙ በርቀቱ ከፍተኛ ልምድና ችሎታ ያላትን እንግሊዛዊቷን አትሌት ላውራ ሙዒርን ቀድማ በመግባት የውድድር ዓመቱ መሪ የሆነውን1:59.49 ሰዓት ማስመዝገብ ችላለች። በሳምንቱ ከተመዘገቡት ታላላቅ ውጤቶች አንዱ የሆነው በስፔን ሳባዴል በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር ገንዘቤ ዲባባ ያስመዘገበችው ነው። የዓለም የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ቻምፒዮንና የርቀቱ የቤት ውስጥም ከቤት ውጪም ክብረወሰን ባለቤቷ ገንዘቤ ዲባባ አሁንም በርቀቱ ከዓለማችን ኮከብ አትሌቶች አንዷ መሆኗን እያሳየች ትገኛለች። ገንዘቤ ምንም እንኳን ወጣ ገባ የሆነ አቋም በማሳየት ያለፈውን የውድድር ዓመት ጎልታ ባትታይም ዘንድሮ 3:59.08 የሆነ ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ሌላኛዋን ኢትዮጵያዊት አትሌት ለምለም ሃይሉን አስከትላ በመግባት ማሸነፍ ችላለች። አዲስ ዘመን የካቲት 2/2011ቦጋለ አበበ ", "passage_id": "50d23e6f5e2cf38f78d5c113c96dbab4" }, { "passage": " ብዙዎች ጥቂቶችን ተከትለው ሃገራቸውን ለማስጠራት ታትረዋል። ሰንደቅ ዓላማ አስታቅፎ በምርቃት የሸኛቸውን ህዝብ አሳፍረው አያውቁም። ከጉዳት መልስ፣ ከወሊድ በኃላ እንዲሁም በጤና መታወክ ተበግረው ከውድድር ማፈግፈግንም አልሞከሩም። የቀንና ሌሊት መፈራረቅ የማያሳስበው የሩጫ ወዳጅም በድጋፉ አብሯቸው ዘመናትን ተሻግሯል። ጥረታቸው ሰምሮ የሃገራቸው ሰንደቅ ኣላማ በድል ከፍ ሲል በደስታ አንብተዋል። ህዝባቸውን በጀግንነት ስለሚያኮሩም በአበባ ጉንጉን ይቀበላቸዋል። ከሽልማትና ስፖንሰር የሚያገኙትን ገንዘብ ሃገራቸው ላይ ፈሰስ በማድረግም ለበርካቶች የስራ ዕድል ፈጥረዋል። እነርሱም ተምሳሌት ያደረጉ ታዳጊዎችም እንደምንጭ ከስር ከስር እየፈለቁ ረጅም ዓመታትን አስቆጥረዋል። ለምስራቅ አፍሪካ ሃገራት በተለይም ለኢትዮጵያ እና ኬንያ የ10ሺህ እና 5ሺህ ሜትር ሩጫ ታላቅ ትርጉም ያለው ነው። ያሉበት የመልካምድር አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ለስኬታማነታቸው እንዳገዛቸው በባለሙያዎች ይነሳል። በግልጽ እንደሚታየው ባለፉት ዓመታት በርቀቶቹ በተካሄዱ ውድድሮች የበላይነቱን የያዙት የሁለቱ ሃገራት አትሌቶች እየተፈራረቁ ነው። በዚህም ምክንያት በአካባቢው እንደ ባህል ስፖርት እንዲታይ ምክንያት ሆኗል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን በእነዚህ ርቀቶች የሚካሄዱ ውድድሮች በዓለም ላይ እየተመናመኑ ነው የሚገኙት። የ10ሺህ\nሜትር ሩጫ በብቸኝነት የሚታየው በዓለም ሻምፒዮና እና ኦሊምፒክ ላይ ብቻ ነው። በዳይመንድ ሊግ ይካሄድ የነበረው የ5ሺህ ሜትር ሩጫም ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ እንደማይካሄድ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር አስታውቋል። ይህም ሃገራቱን ያስቆጣ ሲሆን፤ ቅሬታዎቻቸውን በማንሳት ውሳኔውን ለማስቀልበስ የተለያዩ እርምጃዎችን በመወሰድ ላይ ይገኛሉ። ከሳምንት በፊት በዴንማርክ የተካሄደው የዓለም ሃገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ ጉዳዩን የተቃወሙት ኢትዮጵያ እና ኬንያ በተናጥል የዓለም አቀፉን ማህበር ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮን አናግረዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉም ከፕሬዚዳንቱ ጋር ቆይታ አድርጋለች። በውይይቱ ላይ ካነሷቸው ነጥቦች መካከል አንዱም የ5ሺህ ሜትር ውድድር ጉዳይ አንዱ ነበር። በኦሊምፒክ 10ሺህ ሜትር የመጀመሪያዋ ጥቁር ሴት አትሌት በመሆን አፍሪካን ያስጠራችው ደራርቱ፤ «እኔን እና ሌሎች አትሌቶችን ያሳወቀን 5ሺህ እና 10ሺህ ሜትር ሩጫዎች ናቸው። ኢትዮጵያም የታወቀችበትና የተከበረችበት ይኸው ርቀት ነው። በመሆኑም እንዲህ መሆን የለበትም፤ እኛንም እንደ ህዝብ እና እንደ ምስራቅ አፍሪካ ያስከፋ በመሆኑ በድጋሚ ሊታይ ይገባል» ትላለች። ከማህበሩ ፕሬዚዳንት ጋር በነበራቸው ንግግር ላይም፤ አትሌቶች ወደ ሩጫ ሲገቡ ከ3ሺህ ሜትር በታች ባለው አጭር ርቀት ነው። ከዚያ በኃላ ነው ወደ ማራቶን የሚሄደው። አሁን ግን በቀጥታ ወደ ረጅም ርቀት ለመግባት ይገደዳሉ። ስለዚህም ውሳኔው በድጋሚ ሊታይ ይገባል የሚል ሃሳብ ማንሳቷን ትገልጻለች። በቅርቡ አቢጃን ላይ በሚኖረው ስብሰባ ጉዳዩ የሚነሳ በመሆኑም፤ የሚሆነውን በጋራ እንደምታይም ጠቁማለች። ከዚህ ባሻገር የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን የቦርድ አባል እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆኗ፤ የተለያዩ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደምትገኝ ታስረዳለች። «ከኬንያው የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ጋር በቅንጅት ምን መሰራትና እንዴት መሰራት እንዳለበት በመነጋገር ላይ እንገኛለን። የአፍሪካ ተወካይ እንደመሆናቸው ጉዳዩ ሲወሰን ለምን ዝምታን እንደመረጡ ጥያቄ እናቀርባለን። እነርሱን መተካት ካለብንም ሌሎች ጠንካራና መሞገት የሚችሉ ሰዎችን ከኢትዮጵያም ቢሆን መተካት እንዳለብን እዚያ የምንነጋገር ይሆናል»ም ብላለች። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴም፤ ዓለም አቀፉ ማህበር ከዚህ ቀደም በዳይመንድ ሊግ ይካሄድ የነበረውን የ10ሺህ\nሜትር ሩጫ ማስቀረቱን አስታውሶ፤ እ.አ.አ ከ2020 ጀምሮ\nየኢትዮጵያ አና የአፍሪካ ባህላዊ ሩጫ የሆነውንና በርካታ አትሌቶችም ለራሳቸውና ለሃገራቸው አኩሪ ድል ያስመዘገቡበትን የ5ሺህ ሜትር ሩጫ ከውድድሩ እንደሚቀንስ ማስታወቁን እንደማይደግፍ በመግለጫው ማስታወቁ ይታወሳል። ይህንን በተመለከተም ኮሚቴ በማቋቋም ውሳኔ የማስቀልበስ ስራውን ጀምሯል። በርቀቱ  ታዋቂና ዝነኛ የሆኑ አንጋፋ አትሌቶች በተካተቱበት ኮሚቴ ውስጥም የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዚዳንት ገብረእግዚአብሄር ገብረማርያም አንዱ ነው። ፌዴሬሽኑ እና ኦሊምፒክ ኮሚቴው ከዓለም አቀፎቹ ማህበራት ጋር የሚያደርጉት ግንኙነት እንዳለ ሆኖ የዚህ ኮሚቴ ስራ ድጋፍ መስጠት መሆኑን ይጠቁማል። የኮሚቴው ተግባር ሃሳብ መስጠት ሲሆን፤ ሃገር አቀፎቹ ማህበራትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ሃሳቡን የሚያንጸባርቁ ይሆናል። ገብረእግዚአብሄር ሲያብራራም «5ሺህ ሜትርን ከዳይመንድ ሊግ ማስወጣት ስፖርቱን በጣም የሚጎዳና ለመረሳትም የሚያበቃ ነው። በርቀቶቹ ለዓለም ሻምፒዮና እና ለኦሊምፒክ ብቻ መዘጋጀቱም አስቸጋሪ ይሆናል። ይህንን ተያያዥነት ያለው ስፖርት ማስቀጠል ካስፈለገም 5ሺህ ሜትር መመለስ አለበት የሚለው የፌዴሬሽኑ አቋም ነው። ይህንንም በደብዳቤ ለማህበሩ አሳውቀናል፤ እስካሁን የተባለ ነገር ባይኖርም ወደፊት ግን ምላሽ ይሰጣሉ በሚል ይጠበቃል» ብሏል። የውሳኔ ዜናው እንደተሰማ ከኢትዮጵያም ቀድማ ተቃውሞዋን ይፋ ያደረገችው ጎረቤት ሃገር ኬንያ ነበረች። ነገር ግን በዴንማርክ በተካሄደው የዓለም ሃገር አቋራጭ ሻምፒዮና በኋላ ሃገሪቷ የአቋም ለውጥ ማድረጓን የሚያሳይ ዜና ተሰምቷል። የሀገሪቷ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ከዓለም አቀፉ ማህበር ፕሬዚዳንት ጋር ቆይታ ካደረጉ በኋላ ውሳኔው የተደረሰበት ምክንያት እንዳሳመናቸው ገልጸዋል። ይህ የኬንያዊያን የአቋም መወላወል ኢትዮጵያ የምታቀርበው ተቃውሞ ላይ ተጽእኖ ያሳድር ይሆን የሚለው የብዙዎች ስጋት ነው። አንጋፋው አትሌት ገብረእግዚአብሄር ግን «ተቃውሞው አንድ እና ሁለት መሆኑ ሳይሆን የሚያሸንፈው እውነታው ነው» የሚል\nእምነት አለው። «ወጣቶች\nከአጭር ርቀት በአንዴ ዘለው ማራቶንን መቀላቀል የለባቸውም። በመሆኑም እኛ ደጋፊ ኖረም አልኖረም እውነታውን ይዘን ነው የምንቃወመው። በእነርሱ በኩል የተቃውሞ መቀዛቀዝ ቢኖርም ትክክለኛውን ሃሳብ ይዞ መጓዙ ይሻላል» በማለትም የተቃውሞውን ቀጣይነት ያረጋግጣል።አዲስ ዘመን መጋቢት 30 /2011 ", "passage_id": "3250a503d75327e78d92b138d9603d50" }, { "passage": " በስፖርት የመጨረሻውን ደረጃ ክብር የሚያስገኘው ውድድር ኦሊምፒክ መሆኑ ይታወቃል። በዓለም ትልልቅ ስም ያላቸው ዝነኛ አትሌቶች ሃገራቸውን ወክለው የሚሳተፉበት እንዲሁም በርካታ ክብረወሰኖች የሚሰባበሩበትም ነው። በመሆኑም በአትሌቶች ዘንድ በመድረኩ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ብቻም ሳይሆን ተሳትፎውም ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው።ኦሊምፒክ በየአራት ዓመቱ ስለሚካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት የሚደረግበት ሲሆን፤ ወጥ አቋም የሌላቸው አትሌቶች በተደጋጋሚ ኦሊምፒክ ላይ ሊታዩ አይችሉም። በመሆኑም በርካታ ተሳትፎ ያላቸው አትሌቶችን ለማግኘት አዳጋች ነው። እንግሊዛዊቷ አትሌት ግን በመጪው ዓመት ስድስተኛ የኦሊምፒክ ተሳትፎዋን ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኗን ነው ያሳወቀችው። በተለይ ለወጣት አትሌቶች አስተማሪ የሆነ ተሞክሮዋንም ለቢቢሲ አጋርታለች።ጆ ፓቬ አምስት አሊምፒኮች ላይ የተሳተፈች አንጋፋ አትሌት ስትሆን በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስድስተኛ ተሳትፎዋን በማድረግ የክብረወሰን ባለቤት ለመሆን ፍላጎት አላት። ከዚህ ቀደም የሃገሯ ልጅ የሆነችው ጦር ወርዋሪ ቴሳ ሳንደርሰን ስድስት ኦሊምፒኮች ላይ ሀገሯን የወከለች አትሌት በመባል ተመዝግባለች። ፓቬ ስድስተኛዋን ተሳትፎ የምታደርግ ከሆነ ደግሞ በመም አትሌት የመጀመሪያዋ ትሆናለች።\nፓቬ እአአ በ2014 ከወሊድ በኋላ በአውሮፓ ሻምፒዮና በ10ሺ ሜትር ስትሳተፍ በአንጋፋነቷ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆና ነበር። ይሁን እንጂ በ40ዓመቷ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆን ብቃቷን ማስመስከር ችላለች። በቶኪዮው ኦሊምፒክ ስትሳተፍም ዕድሜዋ 46 ስለሚሆን ምናልባትም በኦሊምፒኩ አንጋፋዋ አትሌት ልትሆን ትችላለች። ፓቬ ለቢቢሲ በሰጠችው አስተያየት ላይም «ዕድሜዬን ረስቼ ስድስተኛውን የኦሊምፒክ ተሳትፎዬን አደርጋለሁ» ብላለች።አትሌቷ ሃገሯን ወክላ በኦሊምፒክ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው እአአ በ2ሺ በተካሄደው የሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ ነበር። «በቶኪዮ የሚካፈለው ብሄራዊ ቡድን ጥሩ ተፎካካሪ እንዲሆን እፈል ጋለሁ። በመሆኑም ዝግጅታችንን ቀድመን መጀመር ይገባናል፤ ፉክክሩ ደግሞ ይበልጥ ደስ የሚያሰኝ ነው» ብላለች። የሁለት ልጆች እናት የሆነችው አትሌቷ ከኦሊምፒኩ አስቀድሞ በዘንድሮው የዶሃ ዓለም ሻምፒዮና አቅሟን የመፈተሽ ፍላጎት እንዳላትም ጨምራ ገልጻለች። እአአ በ2017 በለንደን በተካሄዱት ሁለት ትልልቅ የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ ብትሆንም አልተሳካላትም ነበር። በለንደን ማራቶን ውድድሯን ሳታጠናቅቅ አጋማሽ ላይ ስታቋርጥ፤ በ10ሺ ሜትር በተካፈለችበት ሻምፒዮና ደግሞ በጉዳት ምክንያት ውድድሯን ለማጠናቀቅ አልቻለችም ነበር።ያለፈው ዓመት በተካሄደ ሌላ ውድድር ግን በረጅም ርቀት የመም ላይ ውድድር ሶስተኛ በመሆን የነሃስ ሜዳሊያውን ወስዳለች። በባለቤቷ የምትሰለጥነው አትሌቷ በልምምድ ቦታዎች ላይም ነፍስ ያላወቁ ልጆቿን ይዛ ትሄዳለች «ሩጫ እወዳለሁ፤ የአእምሮ እና ሰውነት ጤናን ለማግኘት ያግዛል። ከቤተሰብህ ጋር ሆነህ ስትከውን ደግሞ ይበልጥ መነሳሳትን ይፈጥራል። ባለቤቴ ያግዘኛል፤ ሥራችንን የምንሰራውም እንደ ቡድን ነው። ሯጭ ስትሆን መጨናነቅን ማስወገድ የግድ ነው ይህም የአእምሮን ጤና ይሰጣል። እድሜህንም እንደ ልምድ መጠቀም ትጀምራለህ» ስትልም የህይወት ልምዷን ታጋራለች።የአትሌቷ የኦሊምፒክ ተሳትፎ በተለያዩ ችግሮች የታጀበ ይሁን እንጂ ተስፋ አለመቁረጧ ግን ለብዙዎች ተሞክሮ የሚሆን ነው። እአአ 1997 ከባድ የሆነና ውስብስብ ቀዶ ጥገና የሚያስፈልገው የጉልበት ጉዳት የደረሰባት ቢሆንም፤ ከዚያ አገግማ በሲድኒ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። እአአ በ2004ቱ የአቴንስ ኦሊምፒክ ከመሳተፏ ሶስት ወራት በፊት የጡንቻ ጉዳት ቢደርስባትም አምስተኛ ደረጃ በመያዝ የዲፕሎማ ተሸላሚ ነበረች።በ2008ቱ የቤጂንግ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሯን ያጠናቀቀችው ደግሞ በውድድሩ ዋዜማ በምግብ መበከል የጤና መታወክ ስለደረሰባት ነበር። በሀገሯ በተዘጋጀው የ2012 ኦሊምፒክ በ5 እና 10ሺ ሜትር ውድድሮች ተሳትፎዋ ሰባተኛ ደረጃ በመያዝም የመጀመሪያዋ አውሮፓዊት አትሌት ተሰኝታለች። በሪዮ በተካሄደው የ2016ቱ ኦሊምፒክ ደግሞ ዘግይታ ውድድሩን በመጀመሯ በ10ሺ ሜትር 15ኛ ደረጃን ነበር የያዘችው። «የሪዮ ኦሊምፒክ ተሳትፎዬ በጣም አስደሳች ነበር፤ አብረውኝ የሮጡት አትሌቶችም ከእኔ በ20ዓመት የሚያንሱ ነበሩ። ቢሆንም ሁሌም ሃገሬን መወከል ለእኔ ኩራት ነው» ስትልም ትገልጻለች።አዲስ ዘመን ጥር 13/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "121a3477a1e1f36d985d4b50ab4afece" }, { "passage": "ይህ ወቅት በአትሌቲክስ ስፖርት የአገር አቋራጭ ውድድሮች በብዛት የሚካሄዱበት ነው። ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻም በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የነሐስ ደረጃ የተሰጠው የቫሌንሺያ አገር አቋራጭ ውድድር ተካሂዷል። በውድድሩም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ ክብረወሰን በመሰባበርም ጭምር አሸናፊ ሆነዋል።በስፔን ዋና ከተማ በተካሄደው በዚህ ውድድር13ሺ ሯጮች ተሳትፈውበታል። 11ሺ የሚሆኑትም የ10ኪሎ ሜትሩን የመጨረሻ መስመር መርገጥ ችለዋል። እጅግ ብርዳማ በነበረው ጠዋት የተጀመረው የሴቶቹ ውድድር ሊሟሟቅ የቻለው በኢትዮጵያዊቷ እና ኬንያዊቷ አትሌት መካከል በነበረው ፉክክር ነው።አትሌት ጸሐይ ገመቹ ከስምንተኛው ኪሎ ሜትር በኋላ ኬንያዊቷን ግሎሪያ ኬትን ጥላት በመሮጥም 30ደቂቃ ከ15ሰከንድ በሆነ ሰዓት የመጨረሻዋን መስመር በመርገጥ አሸናፊነቷን ማረጋገጥ ችላለች። አትሌቷ በአስቸጋሪው የአየር ሁኔታ የገባችበት ሰዓትም የርቀቱን የኢትዮጵያ ክብረወሰን በ15ሰከንዶች ያሻሻለ ሆኗል። አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ርቀቱን 30 ደቂቃ30 በመግባት ለዓመታት ክብረወሰኑን የግሏ አድርጋ ነበር የቆየችው።ፈጣን በነበረው ውድድር እስከ አራት ያለውን ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁት አትሌቶች በሰከንዶች ብቻ በመበላለጥ ከ31ደቂቃ በታች ነበር የሮጡት። የኢትዮጵያዊቷ አትሌት ብርቱ ተፎካካሪ የነበረችው ኬንያዊቷ ግሎሪያ ኬት በበኩሏ በሰከንዶች ዘግይታ 30:26 በሆነ ሰዓት ውድድሩን ለማጠናቀቅ ችላለች። ኬንያውያኑ አትሌቶች ኢቫሊን ቺርቺር እና ሮስመሪ ዋንጂሩ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ሲይዙ፤ 30:43 እና30:50 ደግሞ የገቡበት ሰዓት ነው። በውድድሩ የተካፈለችው ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሁነኛው ይስማን ደግሞ ስድስተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሯን አጠናቃለች።በወንዶች በኩል በተካሄደው ውድድር አሸናፊ የሆነው ኢትዮጵያዊው አትሌት ጫላ ከተማ የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻልም ጭምር ድርብ ክብር አግኝቷል። በአንድ ኪሎ ሜትር 2ደቂቃ ከ43 እና 2ደቂቃ ከ45 ሰከንድ በተሮጠው በዚህ ውድድር ላይ፤ የምስራቅ አፍሪካዎቹ አትሌቶች በመምራት ተጽዕኖ አሳድረው ነበር። ጫላ ከተማ፣ አባይነህ ደጉ እና በተስፋ ጌታሁን ኢትዮጵያን ወክለው፣ በኬንያ በኩል ማቲው ኮፕኮሪር፣ ኤድዋርድ ኪበት፣ ቪዲች ቺሩዮች እንዲሁም በኡጋንዳ በኩል ስቴፈን ኪሳ ከፍተኛ የአሸናፊነት ፉክክር ሲያደርጉ የነበሩ አትሌቶች ናቸው። የርቀቱ አጋማሽ 13ደቂቃ ከ43 ሰከንዶች በሆነ ሰዓት የተሸፈነ ሲሆን፤ ይህም የቦታው የተመዘገበ ፈጣን ሰዓት ነው።ርቀቱን ለማጠቃለል 200ሜትሮች ሲቀሩትም ኢትዮጵያዊው አትሌት ጫላ ከተማ አፈትልኮ በመውጣት27ደቂቃ ከ23ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ የቦታውን ክብረወሰን ጨብጧል። የከዚህ ቀደሙ ክብረወሰን የተያዘው በዓለም ሻምፒዮኑ ማርቲን ፊዝ በገባበት31:36 በሆነ ሰዓትም ነበር። ኡጋንዳዊው ስቴፈን ኪሳ በበኩሉ በአንድ ሰከንድ ልዩነት 27:24 ከመጨረሻው ሊደርስ ችሏል። ኬንያዊው ቪዲች ቺሩዮች 27:26 በሆነ ሰዓት የነሐስ ሜዳሊያ ሲያገኝ፤ ኢትዮጵያዊው በተስፋ ጌታሁን ደግሞ 27:39 በሆነ ሰዓት አራተኛ ሆኗል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አባይነህ ደጉ ሰባተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ፈጽሟል።አዲስ ዘመን ጥር 7/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "0df1614d0e2efe72c3c4d9e759bb35a2" } ]
dd37204af6656536d88b1fc7bda89f01
e39364e17ec77a5d3d11f0901692fc9e
‹‹ወደ ቶኪዮ የምንሄደው ለተሳትፎ ሳይሆን ለማሸነፍ ነው››
ኢትዮጵያ ለኦሊምፒክ ድል አዲስ ባትሆንም ውጤቷ በአትሌቲክስ ብቻ የተገደበ ስለመሆኑ እርግጥ ነው።ተሳትፎዋም ቢሆን ከቦክስ፣ ብስክሌትና ውሃ ዋና ስፖርቶች ያልዘለለ ነው።ጃፓን በመዲናዋ ቶኪዮ ከአራት ወራት በኋላ በምታስተናግደው የ2020 ኦሊምፒክ ግን ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ በሆነ ስፖርት ተሳታፊ መሆኗ ታውቋል።ይህ ብስራት የተሰማው ከኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ስፖርት ሲሆን፤ ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ቱፋ የታሪኩ ባለቤት መሆኑን አረጋግጧል።ሰለሞን ለዚህ ስኬት እንዲበቃ ከስድስት ዓመታት በላይ በአሰልጣኝነት አብሮት የደከመው ማስተር አዲስ ኡርጌሳም ከዚህ ታሪክ ባለቤትነት ጋር አብሮ ይነሳል።በአፍሪካ ካሉ ስመ ጥር የወርልድ ቴኳንዶ አሰልጣኞች ትልቁ ነው።በዓለም አቀፉ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ደግሞ ብቸኛው ኢትዮጵያዊ የአሰልጣኞች እና የዳኞች አሰልጣኝ ነው። የአፍሪካ ወርልድ ቴኳንዶ አሰልጣኞች ሊቀመንበር በመሆንም እያገለገለ ነው።ማስተር አዲስ ዑርጌሳ።በ2010/11 የውድድር ዓመት በተሳተፈባቸው ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ውድድሮች ላይ ባልተመቻቸ ሁኔታ በጥቂት ስፖርተኞች ተሳትፎ 5 ወርቅ 2 ብር እና 3 የነሀስ ሜዳሊያዎች በሚያሰለጥናቸው ስፖርተኞች አማካኝነት ለኢትዮጵያ አስገኝቷል።ባለፈው ሪዮ ኦሊምፒክ የማጣሪያ ውድድሮች በሁለቱም ፆታ ያሰለጠናቸው ተወዳዳሪዎች ወደ ታላቁ መድረክ ለማለፍ ከጫፍ ደርሰው ሳይሳካላቸው ቀርቷል።ከሃያ ዓመታት በላይ በስፖርቱ ውስጥ ያሳለፈው ማስተር አዲስ ዛሬ ላይ ህልሙ እውን ሆኖ ታላቁ የስፖርት መድረክ ላይ ደርሷል።በአገራችን ወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ተስፋና ስጋት እንዲሁም ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ይናገራል። አዲስ ዘመን፡- በዓለም ላይ ስጋት የሆነውን የኮሮና ቫይረስ ተከትሎ ኦሊምፒክ ሊራዘም እንደሚችል ስጋት አለ፣ ምናልባት የሚራዘመው ለረጅም ጊዜ ከሆነ እንደ ወርልድ ቴኳንዶ አይነት ብዙ ልፋትና ዋጋ የሚከፈልባቸው የማጣሪያ ውድድሮች ዳግም ወደ ማጣሪያ የሚገቡበት አጋጣሚ ይኖራል? ማስተር አዲስ፡- አይመስለኝም፤ እስካሁንም እንዲህ የሚል ህግ አላየሁም።ምናልባት ከአንድ ዓመት በላይ የሚራዘም ከሆነ ሊባል ይችል ይሆናል።ነገር ግን አሁን ባለው ሁኔታ እስከ መጨረሻው ነገሮችን ሳይመለከቱ ወደዚህ ውሳኔ ይገባሉ የሚል እምነት የለኝም፤ ቢያራዝሙ እንኳን ጥቂት ወራትን ሊሆን ይችላል የሚል ግምት ነው ያለኝ። አዲስ ዘመን፡- የኦሊምፒክ ማጣሪያውን አልፋችሁ ትልቅ ደረጃ ላይ ስትደርሱ የነበረው ሂደት እንዴት ነበር? ማስተር አዲስ፡- ማጣሪያው ወደ 34 የአፍሪካ አገራት የተሳተፉበት ትልቅ ውድድር ነበር።ለአራት ዓመታት ያደረግነውን ዝግጅትም ከ100 በላይ ከሚደርሱ ስፖርተኞች ጋር ተወዳድረን ነው የመዘንነው።እንደሚታወቀው ሰለሞን ሶስቱን ዓመት እስከ አውሮፓ በመጓዝ በተለያዩ ውድድሮች ላይ ነው ያሳለፈው።በቱርክና በፖላንድ ከተሳተፈባቸው ውድድሮች ባሻገር የአፍሪካ ዋንጫንና ፕሬዚዴንሺያል ዋንጫን ጠቅልሎ በመውሰድ በአፍሪካም ኮከብ በመባል ነበር ያጠናቀቀው።ይህም ወደ ማጣሪያው ሲገባ ትልቅ ደረጃን ይዞ በመሆኑ ውጤቱም መልካም ሆኗል፡፡አዲስ ዘመን፡- ቀደም ባሉት ዓመታት በወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ውጤት ይመጣበታል የሚል ብዙም እምነት አልነበረም፣ ይህን አስተሳሰብ ሰብሮ ፈታኝ የሆኑ ማጣሪያዎችን በማለፍ ለኦሊምፒክ ስፖርተኛን ማብቃት ከባድ መሆኑን መገንዘብ አይከብድም፣ ነገር ግን ይህ ስኬት ትልቅ ቦታ ተሰጥቶታል ብለህ ታምናለህ? ማስተር አዲስ፡- በማጣሪያው ላይ ከሰለሞን ጋር ውድድር ያደረገው ስፖርተኛ በዓመት ውስጥ ከ13 ያላነሱ ውድድሮችን አድርጓል፤ በዓለምና በአፍሪካ ያለው ደረጃም በጣም ጥሩ ነው።ሰለሞን በአንጻሩ ከአራት ያልበለጡ ውድድሮች ላይ ብቻ ተሳታፊ ሆኖ ነው ለአሸናፊነት የበቃው።ይህንን ድል መድገም አይቻልም ነገር ግን የተሰጠው ክብር ብዙም አይደለም። አዲስ ዘመን፡- ከዚህ ቀደም በምትሳተፉባቸው ውድድሮች ብዙም ድጋፍ እንደማይደረግላችሁ ይታወቃል።በዚህ ማጣሪያስ ድጋፉ እንዴት ነበር? ማስተር አዲስ፡- ድሮ ከነበረው በጣም የተሻለ ነበር፤ በተለይ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጥሩ ድጋፍ አድርጎልናል።ፌዴሬሽኑም ያለውን አቅም ተጠቅሟል፤ ከዚህ ቀደም ውድድሮች ሲኖሩብን ለአጭር ጊዜ ነበር ቡድናችንን የምናዘጋጀው አሁን ግን ለረጅም ጊዜ በዝግጅት ላይ እንድንቆይ መደረጉ መልካም ነው።በአንጻራዊነት እንደ አጠቃላይ ያለው ነገር የተሻለ ነው ለማለት ያስችላል።አዲስ ዘመን፡- ማለፋችሁን ተከትሎስ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምን አደረገላችሁ? ማስተር አዲስ፡- እስካሁን ምንም የተደረገልን ነገር የለም፡፡ አዲስ ዘመን፡- ከሰለሞን ባሻገር በአፍሪካ ደረጃ ውጤት ያስመዘገቡ ስፖርተኞች ተስፋ ቢጣልባቸውም አሁን ላይ አናያቸውም ምክኒያቱ ምንድነው? ማስተር አዲስ፡- በእኛ ስፖርት ችግሩ የክለቦች አለመኖር ነው፤ ስለዚህም ወጣቶቹ ስራ ሳይሰሩና ትምህርት ሳይማሩ ስፖርቱ ላይ ብቻ ተሳታፊ እየሆኑ መቆየት አስቸጋሪ ነው።ብዙዎቹ ሰልጣኞች ሌላ ገቢ ስለሌላቸው ከብሄራዊ ቡድን በኋላ ወደ ሌላ ነገር ይሰማራሉ፣ አሊያም ስፖርቱን ይተውታል።ስለዚህም ፌዴሬሽኑ አሁን የመጣው ውጤት ላይ ተመርኩዞ በርካታ ስራዎችን ማከናወንና የማስተዋወቅ ስራ ይጠበቅበታል።በመገናኛ ብዙሃን በኩልም አበረታች የሆኑ ስራዎች በይበልጥ መሰራት ተገቢ ነው።አዲስ ዘመን፡- በኢትዮጵያ እጅግ ተዘውታሪ ከሆኑ ስፖርቶች መካከል የማርሻል አርት ስፖርቶች ተጠቃሽ ናቸው።ነገር ግን በሺዎች ከሚቆጠሩ ተሳታፊዎች ከዓመታት በኋላ ነው አንድ ስፖርተኛ ያገኘነው፤ ምክንያቱ ምንድን ነው? ማስተር አዲስ፡- ከሩቅ ሆኖ ሲታይ ነገሮች ተመቻችተው ይመስላል፤ ነገር ግን እንደ ሌሎች አገሮች ስፖርቱ ኢንቨስት እየተደረገበት አይደለም።ሌሎች አገራት ዝግጅት የሚያደርጉት ለዓመታት ነው፤ በተለያዩ ውድድሮች ላይም ተሳታፊ በመሆን አቅማቸውን ይፈትሻሉ።እኛጋ ግን በዚያ ደረጃ እየሄደ አይደለም፤ ከስር በርካታ ማሰልጠኛ ማዕከላት ይኑሩ እንጂ ከዚያ የሚወጡትን ሰልጣኞች የሚያቅፍ ክለብ የለም።ለአብነት ያህል ከሰለሞን ጋር ዝግጅት የሚያደርግና በእርሱ ደረጃ የሚገኝ ስፖርተኛ ማግኘት ከባድ ነው።ወደ ሌሎች ክለቦች ሄደንም የወዳጅነት ልምምድ ለማድረግም ለእኛ ከባድ ነው።አዲስ ዘመን፡- በቶኪዮ ኦሊምፒክ ላይ የተለየ እቅድ አላችሁ? ማስተር አዲስ፡- ከ20 ዓመት በፊት በተካሄደው የሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ የመገኘት እድል ገጥሞኝ ነበር፤ ወቅቱ ቴኳንዶ የኦሊምፒክ ስፖርት የሆነበት ስለነበር ተጋባዥ በመሆን ነው የታደምኩት።የዚያኔ ለራሴ በኦሊምፒክ ተሳታፊ እንደምሆን ነግሬው ከዓመታት በኋላ ስኬታማ ሆኛለሁ።አራት ኦሊምፒኮችን ከሞከርኩ በኋላም በአምስተኛው እድል ቀንቶኛል።ወደ ቶኪዮ የምንሄደው ደግሞ ለተሳትፎ ሳይሆን ለማሸነፍ ነው።አዲስ ዘመን፡- የአገራችን በርካታ ፌዴሬሽኖች እንኳን ለ20 ዓመታት የአንድ ዓመት እቅድም ሲያወጡና ሲፈፅሙ አይታዩም፣ አንተ በግልህ ይህን አሳክተሃልና ከዚህ ምን መማር ይቻላል? ማስተር አዲስ፡- እኔ በተለያዩ አገራት ተዘዋውሬ እንደተመለከትኩት ከሆነ ለአንድ ስፖርት መሰረትም አስፈላጊውም አሰልጣኝ ነው።አሰልጣኞችን ለማብቃት ደግሞ ፌዴሬሽኖች መስራት ይገባቸዋል፤ ምክንያቱም አሰልጣኝ ሁሌም በልጦ መገኘት አለበት።መንግስትም የፌዴሬሽኖች በጀት ላይ ድጎማ ማድረጉ ተገቢ ነው፤ የሚሰሩትንም ማበረታታት ያስፈልጋል።ሌላው ነገር በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ መሆን ነው፤ ከዚያ በኋላ በደረጃ ወደ ዓለም ማውጣት ይቻላል።አዲስ ዘመን፡- እንዲህ አይነት ስኬቶች ሲመዘገቡ ከእውቅናና ማበረታቻ ጋር በተያያዘ ምን መደረግ ይኖርበታል ትላለህ? ማስተር አዲስ፡- ሁሌም ስለ አንድ ነገር መወራት ያለበት ውጤት ሲመጣ ብቻ መሆን የለበትም።ውጤት ባይመጣም ስፖርተኞች መበረታታት አለባቸው፤ ምክንያቱም በውድድር ዕለት በጥቂት አጋጣሚ ከውጤት ውጪ መሆን ይከተላል።በመሆኑም ውጣ ውረዱና ልፋቱ ሊታይ እንዲሁም ላሉበት ደረጃ በመብቃታቸው ሊበረታቱ ይገባል።ይህ ሲሆን ደግሞ ለቀጣይ መነሳትን ይፈጥራል። አዲስ ዘመን፡- ማስተር አዲስ ለሰጠኽን ጊዜ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡ ማስተር አዲስ፡- እኔም አመሰግናለሁ፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 14 /2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28968
[ { "passage": "በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በእግር ኳስ ለመሳተፍ የአፍሪካ አገራት ሁለተኛውን የደርሶ መልስ የማጣሪያ ጨዋታዎችን ካለፈው ሳምንት ጀምሮ አከናውነዋል። በዋናው ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ አብርሃም መብራቱ እየተመራ ከሁለት ሳምንት ላላነሰ ጊዜ ሲዘጋጅ የቆየው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ኦሊምፒክ ቡድን ማጣሪያውን ሳያልፍ ቀርቷል። ባለፈው ሐሙስ የመጀመሪያውን ጨዋታ በሜዳው ከማሊ አቻው ጋር ያደረገው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ኦሊምፒክ ቡድን አንድ ለአንድ መለያየቱን ተከትሎ ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋው አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ ነበር። እንደ ተሰጋውም ከትናንት በስቲያ ምሽት ወደ ባማኮ አቅንቶ ከሜዳው ውጪ ያደረገውን የመልስ ጨዋታ አራት ለዜሮ ተሸንፏል።በዚህም መሠረት 5ለ1 በሆነ ድምር ውጤት ወደ ቀጣዩ ዙር ሳያልፍ ቀርቷል። እአአ 2004 ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦሊምፒክ እግር ኳስ የተሳተፈችው ማሊ ወደ መጨረሻውና ሦስተኛው ዙር ማጣሪያ ስታልፍ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የመሳተፍ ዕድሏ በጊዜ ከስሟል። ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የማጣሪያ ጨዋታ ሶማሊያን በሜዳዋና በገለልተኛ ሜዳ በሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏ ይታወሳል። ማሊን ጨምሮ አስራ ስድስት የአፍሪካ አገራት ቀጣዩን ዙር መቀላቀላቸውን ካለፈው ሰኞ ጀምሮ አረጋግጠዋል። ያለፈው የአፍሪካ ከሃያ ሦስት ዓመት በታች ዋንጫ አሸናፊዋ ናይጀሪያ ቀጣዩን ዙር ከተቀላቀሉ አገራት መካከል ስትገኝ ሞሮኮ ባልተጠበቀ መልኩ በጊዜ ተሰናባች ሆናለች። ሁለተኛው የማጣሪያ ጨዋታ መጠናቀቁን ተከትሎ ያለፉት አገራት በሦስተኛው ዙር የሚገጥሙትን አገር ማወቅችለዋል። በመጨረሻውና ሦስተኛው ዙር የማጣ ሪያ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ ዚምባቡዌን ስትገጥም ዛምቢያ ከኮንጎ ብራዛቪል፣ጋና ከአልጄሪያ፣ካሜሩን ከቱኒዚያ፣ኮትዲቭዋር ከጊኒ፣ ሱዳን ከናይጄሪያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከማሊ የሚገናኙ ይሆናል። የዓለማችን ትልቁ የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ በሩቅ ምሥራቋ አገር ጃፓን ቶኪዮ ከተማ ሊካሄድ ከሁለት ዓመት ያነሰ ጊዜ ይቀረዋል። በዚህ ኦሊምፒክ ላይ ለመሳተፍ እንደ እግር ኳስ ያሉ የስፖርት ዓይነቶች ረጅም የማጣሪያ ጨዋታዎችን ስለሚሹ ከወዲሁ እየተከናወኑ ይገኛል። በአፍሪካ ዞን ሦስተኛውን የማጣሪያ ጨዋታ የሚያሸንፉ ስምንት አገራት የሚለዩ ቢሆንም በቀጥታ ወደ ኦሊምፒክ አያመሩም። እነዚህ ስምንት አገራት ከዓመት በኋላ ግብፅ ለምታዘጋጀው ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ በቀጥታ የሚያልፍ ይሆናል። በዚህ አፍሪካ ዋንጫ ላይ መሳተፍ ብቻ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚያበቃም አይደለም። በአፍሪካ ዋንጫው ከአንድ እስከ ሦስት ያለውን ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ አገራት በኦሊምፒኩ ተሳታፊ መሆናቸውን ያረጋግጣሉ። የወንዶቹ የኦሊምፒክ ጉዞ እዚህ ላይ ያበቃ ቢሆንም በአሰልጣኝ ሠላም ዘራይ የሚመራው የኢትዮጵያ ሴቶች ኦሊምፒክ ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ምዕራፍ ዝግ ጅቱን በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል። አሰልጣኝ ሠላም ዘራይ በሁለተኛ ምዕራፍ ዝግጅቷ የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ከመሰል ሀገራት ጋር ለማድረግ ያደረገችው ጥረት የተሳካ አይመስልም። ያም ሆኖ የሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ መጋቢት 25 የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታቸውን በአዲስ አበባ ስቴዲየም የሚያደርጉት የኦሊምፒክ ሴቶች ቡድን የመልስ ጨዋታቸውን ከሦስት ቀን በኋላ በዩጋንዳ ካምፓላ የሚያደርጉ ይሆናል። እንስቶቹ በደርሶ መልስ ጨዋታ ድል የሚቀናቸው ከሆነም ቀጣይ ተጋጣሚያቸው ካሜሩን እንደምትሆን ካፍ አሳውቋል። ይህ ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ በግብፅ ሲካሄድ ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን ውድድሩን ለማዘጋጀት ታጭታ የነበረችው ዛምቢያ ነበረች። ይሁን እንጂ ካፍ ይህን ዕድል 2017 መስከረም ወር ላይ ለግብፅ መስጠቱ ይታወሳል። ናይጄሪያ ያለፈው ውድድር ቻምፒዮን መሆኗም አይዘነጋም። በኦሊምፒክ መድረክ በእግር ኳስ የሚሳተፉ ተጫዋቾች ዕድሜያቸው ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የሆኑ ብቻ ቢሆንም አንድ አገር ዕድሜያቸው ከሃያ ሦስት ዓመት በላይ የሆኑ ሦስት ተጫዋቾችን የማሰለፍ ዕድል ይኖረዋል። በሴቶች በኩል ግን በኦሊምፒክ እግር ኳስ ለመሳተፍ የዕድሜ ገደብ አልተቀመጠም። ጃፓን በኦሊምፒኩ የእግር ኳስ ጨዋ ታዎችን ለማስተናገድ በመዲናዋ ቶኪዮ ብቻ ሳትወሰን ሌሎች ከተሞችንም የውድድሩ መዳረሻ ማድረጓ ይታወሳል። ከቶኪዮ በተጨማሪ ኢባራኪ፤ ሴታማ፤ ሳፓሮ፤ ሴንዳይና ዮኮሃማ የእግር ኳስ ውድድሮችን የሚያስተናግዱ ከተሞች ናቸው። ብራዚል ባስተናገደችው የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ በወጣት ቡድኗ አማካኝነት በወንዶች ቻም ፒዮን መሆኗ የሚታወስ ሲሆን ጀርመን በሴቶች ቻምፒዮን መሆን ችላለች።አዲስ ዘመን መጋቢት 19/2011በቦጋለ አበበ", "passage_id": "d6a217a2b323396b881854d75aa583f6" }, { "passage": "በዘንድሮው ክረምት ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ የዓለም ፈተና በሆነው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት የተነሳ ለ2021 እንዲራዘም መወሰኑ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ውስብስብ ፈተናዎች እንደሚገጥሙት የተለያዩ መላምቶችና ትንትኔዎች ከየአቅጣጫው መውጣት ከጀመሩ ሰንብተዋል። ኦሎምፒኩን በቀጣይ ዓመት ለማካሄድ ከተለያዩ ስፖርቶች የማጣሪያ ውድድሮች ጋር በተያያዘ ቁልፍ ጥያቄዎች እየተነሱ ሲሆን ከሌሎች ዓለም አቀፍ ውድድሮች ጋር እንዳይጋጭና የውድድር ቦታዎችን ከማቀናጀት አኳያ ውስብስብ ፈተናዎች ሊገጥሙት እንደሚችሉ ስጋቶች መኖራቸው አልቀረም። የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ቶማስ ባኽ እንደገለፁትም፣ የኦሎምፒኩን መራዘም ተከትሎ በርካታ ጥያቄዎች እየጎረፉ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ በቀጣይ ዓመት ኦሎምፒኩ የሚካሄድበት ወቅት እስኪወሰን ድረስ መጠበቅ የግድ ይሆናል። በኦሎምፒኩ የሚሳተፉ ሰላሳ ሦስት ዓለም አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖች አብዛኞቹ ኦሎምፒኩ ከሰኔ እስከ ሐምሌ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ቢካሄድ ምርጫቸው ነው። የተወሰኑት ፌዴሬሽኖች ደግሞ ከሚያዝያ እስከ ግንቦት እንዲካሄድ ፍላጎት አላቸው። ቶኪዮ የምታስተናግደው ኦሎምፒክ\nየበጋ እንደመሆኑ ከሐምሌ\nወር በፊት ቢካሄድ\nየሌሎች ዓለም አቀፍ\nውድድሮችን መርሃግብር መከለስ\nአንደኛው የቤት ስራ ይሆናል። በዚህ ዓመት ከቶኪዮ ኦሎምፒክ በፊት ሊካሄዱ የታሰቡ በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች መሰረዛቸውና መራዘማቸው ይታወቃል። እነዚህ የተሰረዙ ውድድሮች በቀጣይ ዓመት እንደሚካሄዱ ተስፋ የተደረገ ሲሆን የማይካሄዱ ከሆነ በብዙ መልኩ ኪሳራ እንደሚገጥማቸው ግልፅ ነው። ስለዚህ የራሳቸውን ኪሳራ የሚያሰሉ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች ለኦሎምፒኩ ቅድሚያ የሚሰጡበት እድል ጠባብ መሆን አንዱና ዋነኛው ፈተና እንደሚሆን ስጋት አለ። ኦሎምፒኩ በሚያዝያና ግንቦት የሚካሄድ ከሆነ በቶኪዮ ስጋት ከሆነው ከፍተኛ ሙቀት የሚገላገሉ ስፖርቶች የመኖራቸውን ያህል ፈተና የሚገጥማቸው ሊኖሩ እንደሚችሉ ይጠበቃል። ከሐምሌ መጨረሻ ጀምሮ ሊካሄድ ታስቦ በነበረው የቶኪዮ ኦሎምፒክ ከመሰረዙ አስቀድሞ በዚህ ወቅት ከፍተኛ ሙቀት በመኖሩ የማራቶንና የርምጃ ውድድሮች ወደ ሳፖሮ ከተማ መዛወራቸው ይታወቃል። በቀጣይ ዓመት ሚያዝያና ግንቦት ላይ የሚካሄድ ከሆነ ግን እነዚህ ስፖርቶች ወደ ቶኪዮ የመመለስ እድል ይኖራቸዋል። ይሁን እንጂ ኦሎምፒኩን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ለማስተላለፍ የተዋዋለው የአሜሪካን ኩባንያ በዚያ ወቅት ከምንም በላይ የሚጠብቀው የኤንቢኤና ሌሎች ታላላቅ የአሜሪካን ቅርጫት ኳስ ውድድሮች ስለሚኖሩበት የፍላጎትና የጥቅም ግጭቶች ሊፈጠር ይችላል። ይህ ደግሞ አንዱን ወገን በቢሊየን ዶላሮች ኪሳራ ላይ ሊጥል ስለሚችል ከባድ ፈተና እንደሚሆን ይታመናል። በተመሳሳይ በዚህ ወቅት ከዚህ ዓመት የተላለፉ በርካቶቹ ዓለም አቀፍ ውድድሮች የሚካሄዱበት መሆኑ ሌላ ጣጣ ይዞ መምጣቱ አይቀሬ ነው። በሌላ በኩል እንደ አትሌቲክስ ያሉ ውድድሮች ላይ አትሌቶች የኦሊምፒክ ሚኒማ የሚሰበስቡበት ወቅት እንደመሆኑ የጊዜ መጣበብና ሌሎች መጨናነቆች ይፈጠራሉ የሚል ምክኒያታዊ ስጋት ያሳድራል። ከአትሌቲክስ ውጪ ያሉ ስፖርቶችም ቢሆኑ አትሌቶቻቸው የኦሎምፒክ መስፈርቶችን ማሟላት የግዴታቸው ስለሚሆን ተመሳሳይ እክል ማስተናገዳቸው አይቀርም። ኦሎምፒኩ ከሰኔ እስከ ሐምሌ ቢካሄድ የሚለው ሃሳብ የተሻለ ቢመስልም በርካታ ውስብስብ ፈተናዎች እንደሚጠብቁት መጠቆም ይቻላል። በነዚህ ወራት ከሚካሄዱ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮች መካከል የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናና የዓለም ውሃ ዋና ቻምፒዮና ዋነኞቹቢሆኑም ውድድራቸውን ለመሰረዝ ፍቃደኛነታቸውን መግለፃቸው ይታወቃል። ይህ አበረታችና ለዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተስፋ የሰጠ ቢሆንም በነዚህ አካላት መካከል ተጨማሪ የውል ስምምነት እንደሚኖር ይጠበቃል። ይህ ምናልባትም ሌሎቹ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖችም ለኦሎምፒክ ቅድሚያ እንዲሰጡ ማነሳሳት ቢችልም ወቅቱ በጣም ከፍተኛ ሙቀት የሚኖርበት መሆኑ ለውድድሮች አስቸጋሪ እንደሚሆን ስጋት አሳድሯል። ለዚህም ከሰላሳ ዓመታት በፊት በቶኪዮና ኦሳካ ተካሂደው የነበሩት የዓለም አትሌቲክስ ቻፒዮናዎች ወቅት የነበረውን ሁኔታ ማስታወስ ተገቢ ይሆናል። ይሁን እንጂ ይህ ወቅት ከአሜሪካኖቹ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ውድድሮች ጋር አለመጋጨቱ እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ ሊቆጠር ይችላል። ምንም ይሁን ምንም\nኦሎምፒኩ በመራዘሙ ብቻ\nየጃፓን መንግስትን ጨምሮ\nበርካታ ባለድርሻ አካላት\nከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ\nውስጥ እንደሚገቡ ቀደም\nሲል ተዘግቧል። የጃፓኑ\nኦሎምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም\nገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ\nኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል\nተናግሯል። ዓለም አቀፉ\nኦሎምፒክ ኮሚቴ ለዚህ\nኪሳራ ስጋት ሰላሳ\nሦስቱንም ዓለም አቀፍ\nፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን\nየገባ ቢሆንም በቂ\nእንደማይሆን ታምኖበታል። ፕሬዝዳንቱ\nቶማስ ባኽም ኦሎምፒኩ\nመራዘሙን በገለፁበት ወቅት\nከባድ ኪሳራ እንደሚኖር\nበማመን ሁሉም ባለድርሻ\nአካላት መስዋዕትነት መክፈል\nእንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል።\nከባዱን መስዋዕትነት ማን\nእንደሚከፍልና ጫናው በየትኛው\nወገን ትከሻ ላይ\nሊወድቅ እንደሚችል ግን\nዛሬ ላይ ቆሞ\nበእርግጠኝነት መናገር አይቻልም።አዲስ ዘመን ሐምሌ 9/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "f104e25b8dd0f300cfdb5430c548ea40" }, { "passage": "ቅዳሜ ግንቦት 11 ቀን 2010 ዓ.ም. በሚሊኒየም አዳራሽ ማይንድሴት ኮንሰልት በተባለ ድርጅት የተዘጋጀው የአዲስ አስተሳሰብ ዝግጅት ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ አዲሱን ትውልድ በአሮጌ አስተሳሰብ መምራት አይቻልም አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሳዑዲ ዓረቢያ ያደረጉትን ጉብኝት አጠናቀው ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት እንደ ደረሱ በቀጥታ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ ሲመጡ፣ ዝግጅቱን ለመታደም ለተገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ድንገተኛ ነበር የሆነባቸው፡፡ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተሰባሰቡ በተለያዩ የዕድሜ ክልሎች የሚገኙ ሰዎች ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምረው መሰባሰብ ጀምረዋል፡፡ ቀኑ ዝናባማ ቢሆንም፣ በሬዲዮና በቴሌቪዥን በተደጋጋሚ በመቅረብ በሚታወቁትና የአዘጋጅ ድርጅቱ ባለቤት ምሕረት ደበበ (ዶ/ር) የተዘጋጀው በዓይነቱ ልዩ የሆነ ዝግጅት ላይ ለመታደም፣ ረዣዥም ሠልፎችን ተሰልፈው ወደ አዳራሹ ለመግባት በርካቶች በአዲስ ፓርክ ኃላፊነቱ የተወነ የግል ማኅበር በሚተዳደረው የሚሊኒየም አዳራሽ ተገኝተዋል፡፡በዝግጅቱ ከሰባት ሺሕ እስከ ስምንት ሺሕ ሰዎችን ለማሳተፍ የታቀደ ሲሆን፣ አዳራሹ በታዳሚዎች ሞልቶ ነበር፡፡ የተለየ ሥፍራ የተሰጣቸውም በክብር እንግዶች መቀመጫ ሰገነት ላይ ተቀምጠውም ነበር፡፡በዝግጅቱ ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ሰዎች ቀድመው በድረ ገጽና በአጭር የጽሑፍ መልዕክት እንዲመዘገቡ ማሳሰቢያ የተሰጠ ሲሆን፣ ተመዝጋቢዎች ቀድመው የተመዘገቡባቸውን መረጃዎች በማሳየትና የመግቢያ ወረቀት በመያዝ ነበር ወደ አዳራሹ ሲገቡ የነበረው፡፡ከማይንድሴት ጋር በመተባበር ዝግጅቱን ያሰናዳው ኢቴል አድቨርታይዚንግና ኮሙዩኒኬሽንስ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፣ በድረ ገጽና በአጭር የጽሑፍ መልዕክት የተመዘገቡ ተመዝጋቢዎች በአጠቃላይ አሥር ሺሕ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፣ 6,900 ተሳታፊዎች ወደ አዳራሹ በመግባት ታድመዋል፡፡ ወደ አዳራሹ መግባት የሚቻለው እስከ ዘጠኝ ሰዓት ብቻ እንደሆነ ቢነገርም፣ በዝናብ ምክንያት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ተሳታፊዎች ወደ አዳራሹ ሲገቡ ነበር፡፡ ከዘጠኝ ሰዓት ተኩል በኋላ የመጡ በርካታ ታዳሚዎች መመለሳቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ በድረ ገጽና በአጭር የጽሑፍ መልዕክት ከተመዘገቡና ለመታደም ከቻሉ ተሳታፊዎች በተጨማሪ፣ 500 ተጋባዥ እንግዶችም እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡‹‹እኔ ነኝ አዲሷ ኢትዮጵያ›› በሚል መሪ ቃል የተካሄደውና በዓይነቱ ብዙ ሰዎችን በማሳተፍ የመጀመርያ የሆነው ይህ ዝግጅት አዲስ አገር አዲስ ዕይታ፣ አዲስ አገር አዲስ ትውልድና አዲስ አገር አዲስ አስተሳሰብ የሚሉ ንዑስ ቁልፍ ሐሳቦችን የያዘ  ነበር፡፡ በዝግጅቱ የተለያዩ ሐሳቦችን የያዙ ንግግሮች የተደረጉ ሲሆን፣ የመጀመርያውን ንግግር ያደረጉት ማማ በሰማይ (Tower in the Sky) እና ኃሰሳ (Mine to Win) የተሰኙ መጻሕፍትን የደረሱት ሕይወት ተፈራ፣ ከጣሊያን ሁለተኛው ወረራ አንስቶ እስካሁን ያሉ ትውልዶችን በአራት ከፋፍለው ባህርያቸውን ያሳዩበት ንግግር ‹የትውልድ ክፍተት› ነበር፡፡‹‹ይህ ክፍፍል ሳይንሳዊ እንዳልሆነ እንዲታወቅልኝ፤›› ያሉት ተናጋሪዋ ያሁኑ ትውልድ ግለኝነት የሚያጠቃው፣ ከወላጆቹ ተፅዕኖ የተላቀቀና ራሱን ለመሆን የሚጥር፣ ቴክኖሎጂን ፈጥኖ የተላመደና የሥራ ፈጠራ ባህልን ያዳበረ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ ያለፉት ትውልዶችም በምን ያህል ተፅዕኖ ሥር ያለፉና በኢትዮጵያዊነት ተጠምደው የኖሩ፣ በጣሊያን ጦርነት ወገን ሲያልቅ የተመለከቱ፣ ብሎም የተማሪ ንቅናቄን በአገሪቱ ያስተዋወቁ እንደሆኑ አውስተዋል፡፡ሁለተኛውን ንግግር ያደረጉት የታሪክ ተመራማሪው ኢብራሂም ሙሉሸዋ ሲሆኑ፣ ታሪክና ትውልድ በሚል ርዕስ የታሪክ አስፈላጊነትንና ለምን የግጭት ምንጭ እንደሚሆን ያሳየ ንግግር አድርገዋል፡፡‹‹ታሪክን ስናጠና ፍላጎታችን መሆን ያለበት ለማወቅ ነው፡፡ ጥናቱም በመረጃ ላይ ያተኮረ መሆን አለበት፤›› ያሉት አቶ ኢብራሂም፣ ‹‹በታሪክ የምንገጨው ካለፈው ጠንካራ ኃይልና ብርታትን ለማምጣት ስለሚያግዝ ነው፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡የማይንድሴት ኮንሰልት ባለቤት ምሕረት ደበበ (ዶ/ር)፣ የዝግጅቱ ዋነኛ ትኩረት የሐሳብን ጉልበትና የአስተሳሰብን ኃይል ለማሳየት እንደሆነ፣ ‹‹ሐሳብ ዝም ብሎ ይሥራን ወይንስ ሐሳብን እኛ እንደ ዕቃ ወስደን እንሥራው?›› ሲሉ የዝግጅቱን ጭብጥና ትኩረት ተናግረው ነበር፡፡‹‹ከመንጋ አስተሳሰብ እንውጣና መጀመርያ ግለሰብ እንሁን፤›› ሲሉም፣ እኔ ነኝ አዲሷ ኢትዮጵያ የሚለውን ንድፈ ሐሳብ አስፈላጊነት አስረድተዋል፡፡ ‹‹ከተናጋሪው ይልቅ ምን ተባለ የሚለውን ማሰብና መጠየቅ ያስፈልጋል፤›› ብለዋል፡፡በዝግጅቱ ላይ የክብር እንግዳ እንደሚኖር የተነገረ ቢሆንም፣ ማንነታቸው ሳይገለጽ ቆይተው በዝግጅቱ ማብቂያ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ለዝግጅቱ ልዩ ገጽታ የሰጡት ሲሆን፣ ተሳታፊዎች እሳቸው ወደ መድረኩ ሲወጡ በፉጨት፣ በጭብጨባና በጩኸት አዳራሹን ሲያናውጡ ነበር፡፡ከመካከለኛው ምሥራቅ ሁለት አገሮች ጉብኝት በኋላ ቀጥታ ወደ አገር ውስጥ እንደገቡ ወደ አዳራሹ የመጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕዝቡን አመሥግነው፣ በጉብኝታቸው ወቅት የነበሩባቸው አገሮች ስላዩት ነገርና ስላከናወኗቸው ጉዳዮች፣ በተጨማሪም  ስለራዕይ አስፈላጊነት ንግግር አድርገዋል፡፡‹‹ይህ ዝግጅት ከአራት ወራት በፊት የታቀደ ነበር፡፡ … አሁን ግን በአዲሱ ማንነት ነው የምናገረው፣›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ጉብኝት ባደረጉባቸው አገሮች በቅድሚያ በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንዲፈቱ ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን፣ የዜጎችን ጉዳይ ማስቀደማቸው በሄዱባቸው አገሮች መንግሥታት ያስገኘላቸውን ተቀባይነትና አድናቆት አጉልተው ተናግረዋል፡፡‹‹በሄድንበት አገር ምን ትፈልጋላችሁ ስንባል ገንዘብ ሳይሆን ዜጎቻችንን ፍቱልን አልን፡፡ ያ ሲሆን ደግሞ ያልጠየቅነው ሁሉ ይሰጣል፤›› ሲሉም ዜጎችን ከእስር እንዲፈቱ ማድረጋቸው፣ እንዴት ሌሎች ውጤቶች እንዳስገኘላቸው አስረድተዋል፡፡‹‹ኢትዮጵያ ከ70 በመቶ በላይ በዕድሜ አዲስ የሆነ ትውልድ ስላላት፣ ይኼንን ትውልድ በአሮጌ አስተሳሰብ መምራት አይቻልም፤›› ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ‹‹ለኢትዮጵያ ሕዝብ አዲስ ራዕይ ማካፈል ያስፈልጋል፤›› ብለዋል፡፡‹‹አዲስ ነገር የሰው ልጅ ሲፈልገው የኖረው ነው፡፡ በዚያው ልክ የሰው ልጅ አዲስ ነገር ይፈራል፡፡ ሰው በትናንት ውስጥ ተሸብቦ የሚኖረው ለአዲስ ነገር ባለው ፍርኃት ነው፡፡ ይኼንን ማሸነፍ የሚቻለው አዲስ ሐሳብ በማምጣት ነው፤›› ብለዋል፡፡‹‹በአገሪቱ እየታየ ባለው ለውጥ ምክንያት ሳዑዲ ዓረቢያ በብዙ መንገድ ኢትዮጵያን ለመደገፍ መነሳቷን፣ ስንደመር ምን ያህል ክብር እንዳለን ያየንበት ጊዜ ነው፤›› ሲሉም ተናግረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራዕይ ለመሪነት ምን ያህል አስፈላጊ ነው የሚለውን ሲያወሱም፣ ‹‹ራዕይ የሌለው መሪ ነጂ መሆን ይችላል እንጂ መሪ ሊሆን አይችልም፡፡ ፍጻሜውን የማያውቅ ከንቱ ተጓዥ ነው፤›› ብለዋል፡፡የፖለቲካና የፖሊሲ መሪዎች ከመምራት ባለፈም መመራትን ልምድ ማድረግ እንዳለባቸውና የሞራል፣ የመረጃ፣ የዕውቀት፣ የጥበብ፣ የሐሳብ፣ የጤና፣ የቤተሰብ፣ የሰላምና የፍትሕ መሪዎች ከፖሊሲ መሪናዎች እኩል አገር በመምራት ላይ ያላቸው ሚና ከፍተኛ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡‹‹ኢትዮጵያ ካርታ ካርታዋን የምንፈልግ፣ ዜጋ ዜጎቿን የማንፈልግ መሆን የለባትም፤›› በማለትም የግለሰቦችን ሚናና አስተዋፅኦ ዕውቅና ሰጥተዋል፡፡ በሚሊኒየም አዳራሽ የነበረው ዝግጅት ላይ ከታደሙት መካከል ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ አንዱ ሲሆን፣ ለዝግጅቱ ‹‹የተጋነነ ግምት›› ኖሮት ሳይሆን ‹‹በጉጉትና ምን ይሆናል?›› የሚለውን ለማወቅ በሥፍራው እንደተገኘ፣ ሆኖም የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ በአዳራሹ መገኘት ያልጠበቀውና እንዳስደሰተው ለሪፖርተር ተናግሯል፡፡‹‹የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ወደፊት ራዕይ ላይ ያተኮረ ነበር፣ ንግግራቸውም ጥሩና አነቃቂ  ንግግር ነበር፤›› ብሏል፡፡ ይሁን እንጂ በዶ/ር ምሕረት የቀረበው ንግግር ያልተቋጨ እንደነበር፣ ሆኖም አነቃቂ ንግግር እንዳደረጉ ጠቁሟል፡፡‹‹ከተማው ውስጥ ያሉ ልሂቃን ወጣቶች ተገኝተዋል ብዬ አስባለሁ፡፡ ከንግግሮቹም ይልቅ በሕዝቡ ውስጥ የነበረው ተስፋ ነው የሚያስደስተው፤›› ሲልም ተሳታፊዎች የፈጠረባቸውን ስሜት ገልጿል፡፡ ‹‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ መምጣት ሕዝቡ ያሳየው ደስታ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ተቀባይነት እያገኙ መሆናቸውን ያሳያል፡፡ ካሁን በፊት ሲያገኙት የነበረው በፖለቲካ ፓርቲ ተለይተው የመጡ ሰዎችን ነው፡፡ ይኼኛው ግን የተለያዩ አካላትን ያገኙበት ነበር፤›› ሲል በተሳታፊዎች ላይ የነበረውን ዕይታ አጋርቷል፡፡በተመሳሳይ በዝግጅቱ ላይ ተሳታፊ የነበሩት የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) አባልና የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ልደቱ አያሌው፣ ‹‹እንዲህ ዓይነት ዝግጅቶች አስፈላጊ ናቸው፡፡ አስተሳሰብን በሚመለከት መደረግ ስላለባቸው ነገሮች፣ የአስተሳሰብ ጥራትና ምክንያታዊነት ላይ፣ ከመንጋ አስተሳሰብ ወጣ ብለው ሰዎች በራሳቸው እንዲያስቡ የሚረዳ ዝግጅት ነው፤›› ሲሉ ከሪፖርተር ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል፡፡ዝግጅቱ አሁን ካለው የአገሪቱ ሁኔታ ጋር የሚሄድ፣ በተለይም ጽንፈኝነት በበዛበት ጊዜ ይኼንን ዓይነት መድረክ ማዘጋጀት ትልቅ ጥቅም አለው ብለው እንደሚያምኑም ገልጸዋል፡፡‹‹ምክንያታዊነት ባለመኖሩ፣ የአስተሳሰብ ፖለቲካ ባለመዳበሩና ይኼንን መፍጠር ባለመቻላችን ነው ጽንፈኝነት የበዛው፤›› የሚሉት አቶ ልደቱ፣ ‹‹ይህ ዓይነቱ ሥራ ባለመሠራቱ ነው የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ እንዲህ አስቸጋሪ የሆነው፤›› ብለው እንደሚያምኑ አስታውቀዋል፡፡ዝግጅቱ የመጀመርያ እንደመሆኑ መጠን የጠበቁትን ያህል ሆኖ እንዳላገኙት የገለጹት አቶ ልደቱ፣ ‹‹ጥሩ ጅምር ነው፣ የተነሱት ርዕሶችም ጥሩ ነበሩ፤›› ብለዋል፡፡አቶ ልደቱ በተመሳሳይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ መምጣት ድንገተኛ እንደሆነባቸውና ‹‹ትልቅ ነገር›› እንደሆነ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያደረጉትም ንግግር በእሳቸው ዕይታ ጥሩ እንደነበርም አውስተዋል፡፡‹‹የመጡት ተሳታፊዎች በብዛት ወጣቶች ናቸው፡፡ ከቢዝነስ ማኅበረሰቡም የመጡ አሉ፡፡ ስለዚህ ይህ ነገር ትልቅ የአገር ፕሮጀክት መሆን አለበት፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡የአስተሳሰብ ጉዳይ ለአገሪቱ ፖለቲከኞች ትልቅ ፈተና መሆኑን፣ የሚጠይቅና በምክንያት የሚያምን ማኅበረሰብ መፍጠር ለአገር ጠቃሚ እንደሆነ አሳስበዋል፡፡‹‹የአገሪቱ የትምህርት ሥርዓትም በዚህ መንገድ መቃኘት አለበት፡፡ እንዴት እንደሚታሰብ የሚያሳይ ትምህርትና ፈተና ጭምር ተዘጋጅቶ መሠራት አለበት፤›› ብለው እንደሚያምኑም ገልጸዋል፡፡ ‹‹ጭንቅላትን መጠቀም የሚስችል ሥርዓተ ትምህርት ያስፈልጋል፤›› ብለዋል፡፡ዝግጅቱ ነፃነት የሚሰማቸውንና የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ መሆኑ የተለያዩ አስተሳሰቦችን ለማስተናገድ እንደሚረዳ ገልጸው፣ ‹‹ከመድረክ የሚቀርቡ ነገሮችም እንደዚሁ የተለያዩ ሐሳቦችን የሚያንፀባርቁ መሆን አለባቸው፤›› ብለዋል፡፡በተመሳሳይ ይኼ ዝግጅት ጥሩ ነው ብሎ የሚያምነው በፍቃዱ፣ ስኬታማ ሰዎች ተሞክሮዎቻቸውን ቢያቀርቡና ልምድ ቢያካፍሉ እንደሚመርጥና በሥራዎቻቸው ስኬታማ የሆኑ ሰዎችን ለማየት ተናግሯል፡፡በዝግጅቱ ማጠናቀቂያ ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ፣ መንግሥት ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የወርቅ ተሸላሚ ሆነው የሚመረቁ ተማሪዎችን በቤተ መንግሥት (በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት)፣ በፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና በሌሎች እንደ ኢንዱስትሪ ፓርክ ባሉ የልማት ማዕከላት ልምድ እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በፈለጉበት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉና አገራቸውን ማገልገል እንዲችሉ የሚያደርግ አዲስ ፕሮጀክት፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እንደሚጀመር ተናግረዋል፡፡‹‹በጠቅላይ ሚኒስትር ስኮላርሺፕ በምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲማሩ ይደረጋል፡፡ ቤተ መንግሥት የማንም ሕልመኛ እንጂ የተለዩ ሰዎች ሥፍራ እንዳልሆነ ታያላችሁ፤›› ሲሉም ተናግረዋል፡፡የትምህርት ጥራቱን ለማሳደግም በትኩረት እንደሚሠራ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡‹‹በትምህርት ብዙ መዋዕለ ንዋይ እያፈሰስን ነው፣ ነገር ግን በምንም መለኪያ ብዛት ጥራትን ሊተካ አይችልም፤›› ሲሉም ካሁን በኋላ የመንግሥት ትኩረት ጥራት ላይ እንደሚሆንና ተመራቂዎች ‹‹ተመርቆ መመረጥ የማይችል›› ዜጋ እንዳይሆኑ ብዙ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡አገር ለመምራት ነገን የማየት ራዕይ እንደሚያስፈል የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹ዛሬ ላይ ሆነን ነገን ማየት ስንችል ነው አዲስ ነገር ማምጣት የምንችለው፡፡ ልበ ብርሃን መሆንና ስትወጡ መውረድ እንዳለ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ ራዕይ ያለው ሰው ፍፃሜውን ማየት የሚችል መሆን አለበት፤›› ብለዋል፡፡የማይንድሴት ዝግጅት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ በፋና ቴሌቪዥንና በሸገር ኤፍኤም ሬዲዮ በቀጥታ ሥርጭት የተላለፈ ሲሆን፣ በአዳራሹ ተገኝተው መከታተል ላልቻሉና ፍላጎት ለነበራቸው ሰዎች ታስቦ የተደረገ እንደሆነ የዝግጅቱ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡በድምፃዊ ስለሺ ደምሼ (ጋሽ አበራ ሞላ) መድረክ መሪነት የተካሄደው ዝግጅት በማይንድሴት ባንድና በመሶብ ባንድ የደመቀ ነበር፡፡ ‹ሕልሞቻችሁን ፈልጉ› የሚል ግጥም ለማሰማት ዕቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ መምጣት ምክንያት ግጥሙ ሳይተላለፍ ቀርቷል፡፡ የአዘጋጁ ድርጅት ኃላፊ ንግግርም በዚሁ ምክንያት ያለመቋጫ ተጠናቅቋል፡፡በየሦስት ወሩ አንዴ እንደሚካሄድ ዕቅድ የተያዘለት ይኼ ዝግጅት፣ በቀጣይ ከአዲስ አበባ ውጪ በክልል ከተሞች በተለየም በሐዋሳ፣ በጅማ፣ በባህር ዳርና በሌሎችም ከተሞች እንሚዘዋወር ተጠቁሟል፡፡", "passage_id": "c1f956dc86d47e732a2688b8f08ca8e9" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በበጃፓን ቶኪዮ ለሚካሄደው ኦሊምፒክ የሚደረጉ ዝግጅቶችን ለማስተባበር ከተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ጋር ተወያዩ።በውይይቱ ወቅት ኮሚቴው ለቶኪዮ ኦሊምፒክ እያደረገ ያለውን ዝግጅት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል።በውድድሩ ከተሳትፎ ባለፈ አትሌቶች በድል እንዲመለሱ የማገዝ አላማ እንዳለው መግለጹን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2020 በሚካሄደው የጃፓን ቶኪዮ 32ኛው የኦሎምፒክ ውድድር በአትሌቲክስ፣ በቦክስ፣ በእግር ኳስ፣ በብስክሌት፣ በውሃ ዋና፣ በካራቴ፣ በወርልድ ቴኳንዶና ዒላማ ተኩስ ስፖርቶች ለመሳተፍ እቅድ ይዛለች።በተደረጉ ግምገማዎች ቅርጫት ኳስና እጅ ኳስ ውድድሮች ከሌሎቹ ከታቀዱት 8 ስፖርቶች በተጨማሪ በእቅድ ውስጥ ለማካተት ሀሳብ እንዳለ ከኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።ኢትዮጵያውያን ተወዳዳሪዎች በተለያዩ ስፖርቶች በቶኪዮ ኦሊምፒክ ውድድር አገራቸውን ወክለው መሳተፍ በሚያስችላቸው የማጣሪያ ውድድሮች ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ።", "passage_id": "327e1a68b49e3617606a3ca14468b3d3" }, { "passage": "በዓለም ላይ የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) ተከትሎ ታላቁን የኦሊምፒክ ውድድር (ቶኪዮ 2020) ጨምሮ በዓለም ላይ በርካታ ስፖርታዊ ኩነቶች የመሰረዝና የመራዘም ዕድል ገጥሟቸዋል:: በርካቶቹ የተራዘሙ ወይም የተሰረዙ ውድድሮች በዘንድሮው ዓመት ሊካሄዱ ቀጠሮ የተያዘላቸው ናቸው:: ለመጀመሪያ ጊዜ ከሁለት ዓመት በኋላ ምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ሴኔጋል በመዲናዋ እንደምታዘጋጀው ሲጠበቅ የነበረው የ2022 የወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ ወደ 2026 እንዲራዘም መወሰኑ ያልተጠበቀ ሆኗል:: የውድድሩ ባለቤት የሆነው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ይህን ውድድር ለአራት ዓመታት ማራዘሙን የገለፀ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ሊካሄድ የነበረው ውድድር የተራዘመው የአዘጋጅ አገሯ ሴኔጋል ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት መሆኑ ታውቋል:: ጥያቄውን የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ከተወያየበት በኋላ ውድድሩን ለአራት ዓመት ማራዘሙ ተገልጿል:: የወጣቶቹን ኦሊምፒክ ለማራዘም ውሳኔ ላይ የተደረሰው የቶኪዮ\n2020 ኦሊምፒክ ለአስራ ስድስት ወራት መራዘሙን ተከትሎ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች፣ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖችና ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ራሱ የውድድር ጫናዎች ስለተደራረቡበት መሆኑ ተጠቁሟል:: የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ሴኔጋል በመዲናዋ የምታስተናግደው የወጣቶች ኦሊምፒክ በታቀደበት ጊዜ እንዲካሄድ መፍቀድ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው በሦስት ዓመታት ውስጥ አምስት ታላላቅ ውድድሮችን እንዲያካሂድ ማድረግና ጫና መፍጠር መሆኑን ተናግረዋል::‹‹ ይህን መፍቀድ በሁሉም ባለድርሻ አካላት ላይ ከባድ የሥራ ጫና መፍጠር ነው›› ሲሉም ገልፀዋል:: የዳካርን 2022 የወጣቶች ኦሊምፒክ ማራዘም የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ጨምሮ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በመራዘሙ ከሚፈጠርባቸው ጫና በመጠኑም ቢሆን ነፃ ሆነው የተሻለ በማቀድ እንዲንቀሳቀሱ ሊረዳቸው እንደሚችል ተነግሯል:: ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖችና ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች የቶኪዮ ኦሊምፒክ በመራዘሙ ሳቢያ የውድድር መደራረብና የሥራ ጫና እንደሚኖርባቸው ከመታመኑ ባሻገር በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ሳቢያ የፋይናስ ቀውስ እንደሚገጥማቸው የተለያዩ መረጃዎች ይጠቁማሉ:: ዳካር በዓለም የመጀመሪያ የሆነውን የወጣቶች ኦሊምፒክ እንድታዘጋጅ እ.ኤ.አ 2018 ላይ ይሁንታ ያገኘች ሲሆን ለአፍሪካ ትልቅ ዕድል መሆኑ በወቅቱ ተነግሯል:: ለውድድሩ አስፈላጊው በጀት ከኮሮና ቫይረስ መከሰት ጋር ተያይዞ የሴኔጋል መንግሥት ማቅረብ እንዳልቻለ ታውቋል:: ይህን ውድድር ወደ 2026 ማራዘም በተመሳሳይ ዓመት በሚላንና ኮርቲና አምፔዞ ከሚካሄዱት የክረምት ኦሊምፒክና ፓራሊምፒክ ውድድሮች ጋር እንደሚጋጭም ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃ አስተያየት እየሰጡበት ነበር:: ባኽ በበኩላቸው ይህን ውድድር በ2026 እንዲካሄድ ሲወሰን ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ሌሎች አገራትን የማወያየት ጊዜ እንዳላገኘና ይቃወማሉ የሚል እምነት እንደሌለውም አስተያየት ሰጥተዋል:: ውድድሩ ምናልባትም ከሴኔጋል ተነጥቆ ለሌሎች አገራት ሊሰጥ እንደሚችል የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ኮሎምቢያ፣ ሕንድ፣ ሩሲያና ታይላንድ ውድድሩን ለማዘጋጀት ፍላጎት ከማሳየታቸው በተጨማሪ ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጋር ንግግር መጀመራቸው ታውቋል:: እነዚህ አራት አገራት ውድድሩን በ2030 ለማዘጋጀት ቅድሚያ ሊያገኙ እንደሚችሉ እንጂ የዳካር ዕድል ተነጥቆ እንደማይሰጣቸው ባኽ አስረድተዋል:: የሴኔጋሉ ፕሬዚዳንት ሳል የወጣቶቹን ኦሊምፒክ በተራዘመበት ወቅት 2026 ላይ አገራቸው ለማዘጋጀት ፍላጎቱ እንዳላት የተገለፁ ሲሆን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴም ውድድሩን ዳካር ላይ ለማድረግ ከሴኔጋል አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያገኝ ቃል ገብተዋል:: ፕሬዚዳንቱ አክለውም ዳካር ይህን ዕድል ዳግም የምታገኝ ከሆነ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳካ የወጣቶች ኦሊምፒክ ውድድር እንደምታሰናዳ ተናግረዋል:: ታላቋ አህጉር አፍሪካ ብዙ ጊዜ በስፖርት መድረክ ታላላቅ አውራ ውድድሮችን የማዘጋጀት ዕድል ሲገጥማት አይስተዋልም። ለዚህም ከአቅምና ሌሎች ተያያዥ ችግሮች ጋር ተያይዞ አህጉሪቱ እንደማትችል አድርጎ መቁጠር ዋናው ምክንያት ነው። እ.ኤ.አ 2010 ላይ ደቡብ አፍሪካ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫን በተሳካ ሁኔታ ካስተናገደች ወዲህ ይህ የተሳሳተ አመለካከት በጥቂቱም ቢሆን ተስተካክሏል ማለት ይቻላል። ለዚህም እንደ ሞሮኮ ያሉት አገራት በቅርቡ የዓለም ዋንጫን ለማስተናገድ ካደጉት አገራት ጋር ጨረታ ውስጥ ሲገቡ ለማየት ተችሏል። ኦሊምፒክ የዓለማችን ትልቁ የስፖርት መድረክ እንደመሆኑ መጠን አፍሪካውያን በተሳትፎ እንጂ በአዘጋጅነት ምን እንደሚመስል ተመልክተውት አያውቁም። አሁን ግን ይህን ታላቅ መድረክ በራሳቸው ምድር ደግሰው ሌሎችን የሚጋብዙበት መንገድ እየተጠረገ የመጣ ይመስላል። 2018 ላይ በአርጀንቲና ቦነ ሳይረስ በተካሄደው ሰላሳ ሦስተኛው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ሴኔጋል እ.ኤ.አ በ2022 የሚካሄደውን አራተኛውን የወጣቶች ኦሊምፒክ ለማዘጋጀት በሙሉ ድምጽ የምርጫ ውጤት በይፋ መረከቧ ይታወሳል:: በዘመናዊው ኦሊምፒክ 122 ዓመታት የውድድር ታሪክ አዘጋጅነቱ ወደ አፍሪካ አህጉር ሲመጣ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው:: ሴኔጋል ይህንን ዕድል ያገኘችው ከሌሎች ሦስት የአፍሪካ አገራት ማለትም ከቱኒዚያ፡ ናይጀሪያ እና ቦትስዋና የቀረበባትን ከባድ ፉክክር አሸንፋ እንደሆነም ይታወሳል::ሴኔጋል ለዚህ ውድድር ሲባል አዲስ የተገነባች ከተማን ጨምሮ ለውድድሩ ሦስት ከተሞችን በማዘጋጀት በወጣቶች ብዛት ቀዳሚ የሆነችውን አህጉራቸውን አፍሪካን የሚያኮራ ዝግጅት እንደምታደርግ ቃል ገብታ ነበር:: ለዚህ ውድድር ሲባልም አዳዲስ ዘመናዊ ባቡሮችና ሃምሳ ሺ ሰው የሚይዝ ስቴድየም ለመገንባትም አስባ ነበር:: የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አፍሪካ የኦሊምፒክ ውድድሮችን እንድታዘጋጅ ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ፍላጎት የነበረው ሲሆን ደቡብ ኮሪያ ፒዮንግያንግ ተዘጋጅቶ የነበረውን የክረምት ወራት ኦሊምፒክ አፍሪካ እንድታዘጋጅ ፍላጎት እንደነበረው ይታወሳል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ይህ ዕድል ለአፍሪካ መሰጠቱ ወደ ፊት ዋናውን የበጋ ወራት ኦሊምፒክ በአፍሪካ ለማዘጋጀት ዕድል እንደሚፈጥር በመናገር «ጊዜው የአፍሪካ ነው» አይዘነጋም። የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ስምንተኛው ፕሬዚዳንት ጃክ ሮጅ ሃሳብና ውጤት የሆነው እድሜያቸው ከ15-18 ያሉ ወጣቶች ብቻ የሚሳተፍበት የወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ እ.ኤ.አ 2010 ሲንጋፖር ላይ የተጀመረ ሲሆን ዋነኛ አላማው በአገራት መካከል ውድድሮች ገዝፈው ሜዳሊያዎችን መሰብሰብ ሳይሆን ወጣቶችን በስፖርት እንዲሳተፉ ማነሳሳት፣ በኦሊምፒክ እሴቶች ላይ የተመሰረተ ኑሮ እንዲኖሩ ማበረታታት እና የኦሊምፒዝም ፍልስፍና አምባሳደር እንዲሆኑ ማድረግ ነው። እነዚህ አምባሳደሮች ተቀራርበው የየአገራቸውን ባህል፣ ትውፊትና እና ወግ የሚከፋፈሉበት ብሎም በልዩነታቸው ውስጥ አንድነታቸው ጎልብቶ በኦሊምፒዝም አተያይ ተቻችለው እና ተከባብረው ይህችን ዓለም የተሻለችና ተፈቃቅረው የሚኖሩባት ሰላማዊ መንደር ማድረግ ነው:: ይህንን አላማ አንግቦ ሲንጋፖር ላይ የተጀመረው የዓለም ወጣቶች ኦሊምፒክ ለሁለተኛ ጊዜ በቻይና ናይንጄ ላይ ተካሂዶ ተራውን ለአርጀንቲናዋ መዲና ቦነስ አይረስ መስጠቱ ይታወቃል።አዲስ ዘመን\nሐምሌ 18/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "6b5a3d30f5d37bd9141986108a66635e" } ]
6422e0e1a1c7d16245886023e13e7eb6
b85919181fd350bdcb22f9068b06c95f
ካናዳ ከቶኪዮ ኦሊምፒክ እራሷን አገለለች
ካናዳ በኮሮና ቫይረስ ስጋት በዚህ ዓመት ይካሄዳል ተብሎ ከሚጠበቀው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ራሷን ማግለሏን ቢቢሲ ዘግቧል። ጃፓን ለማስተናገድ ለዓመታት ስትዘጋጅለት የነበረው የ2020ው ኦሊምፒክ ውድድር ከአራት ወራት በኋላ በሐምሌ ወር የሚካሄድ ቢሆንም በቫይረሱ ስርጭት ሳቢያ ላይካሄድ እንደሚችል ስጋት አድሯል፡፡ ኦሊምፒኩ ይካሄድም አይካሄድም በዓለም አቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ በሆነው የኮሮና ቫይረስ ስጋት ምክንያት ካናዳ ከኦሎምፒክ መድረክ ራሷን ከወዲሁ ማግለሏ ተረጋግጧል፡፡ የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ለመጀመሪያ ጊዜ የኦሊምፒክ ውድድሩ ለሌላ ጊዜ ሊተላለፍ እንደሚችል ከተናገሩ በኋላ ካናዳ ይህንን ውሳኔዋን ልትወስን መቻሏን የዘገበው ቢቢሲ ፤ካናዳ የጨዋታው ዋነኛ ተሳታፊ ከሚባሉት መካከል መሆኗን ገልጾ ፤እራሷን በማግለሏ በውድድሩ መካሄድ ላይ ተጨማሪ ጥርጣሬ ፈጥሯል ብሏል። የካናዳ የኦሊምፒክና ፓራኦሊምፒክ ኮሚቴ ውሳኔውን በተመለከተ እንደገለፀው፤ ከውድድሩ ለመውጣት ከውሳኔ ላይ ከመድረሱ በፊት ከአትሌቶች፣ ከስፖርት ቡድኖችና ከካናዳ መንግሥት ባለስልጣናት ጋር ተመካክሯል፡፡ ኮሚቴው ጨምሮም ለዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ ለዓለም አቀፉ የፓራኦሊምፒክ ኮሚቴና የዓለም የጤና ድርጅት የኦሊምፒክ ውድድሩ በአንድ ዓመት እንዲዘገይ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል። «ውድድሩን ለሌላ ጊዜ በማሸጋገር ሂደት ውስጥ የሚያጋጥመውን ውስብስብ ሁኔታን ብንረዳውም፤ ምንም ነገር ከአትሌቶቻችንና ከዓለም ሕዝብ ጤናና ደህንነት የሚበልጥ አይሆንም» ሲል የካናዳ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫም አስታውቋል። ካናዳ በኦሊምፒክ መድረኩ አልሳተፍም ማለቷን ተከትሎ የአውስትራሊያ የኦሊምፒክ ቡድን ውሳኔውን በመደገፍ መግለጫ ማውጣቱን ቢቢሲ አስነብቧል። የአውስትራሊያ የኦሊምፒክ ቡድን እንዳለው አሁን ባለው ሁኔታ ውድድሩ በተያዘለት ጊዜ እንደማይካሄድ ግልጽ እየሆነ በመምጣቱ ተሳታፊ አትሌቶች ለቀጣዩ ዓመት እንዲዘጋጁ ተነግሯቸዋል። አዲስ ዘመን መጋቢት 15/ 2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29026
[ { "passage": " በዓለም ላይ ታላላቅና ዝነኛ የጎዳና ላይ ውድድሮች በአብዛኛው በጥቅምት ወር ይካሄዳሉ። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆነውና በሰሜናዊው የአሜሪካ ክፍል በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ ከተሰጣቸው አራት ማራቶኖች መካከል አንዱ የካናዳው ቶሮንቶ ማራቶን ነው። በተለያዩ ርቀቶች በሚካሄደው በዚህ የጎዳና ላይ ሩጫ ከ50 ሃገራት የተወጣጡ 26ሺ የሚሆኑ አትሌቶችና ጎብኚዎች እንደሚሳተፉበት ይጠበቃል። በዚህ ማራቶን ላይ በርካቶች ፈጣን እና ምርጥ ሰዓት የሚያስመዘግቡበት በመሆኑ እንዲሁም ለቦስተን ማራቶን እንደ መግቢያ ስለሚታይ በርካታ ታዋቂ አትሌቶች ይሳተፉበታል። በቀጣዩ ወር አጋማሽ በሚካሄደው 20ኛው ዙር ውድድር ላይም ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ታውቋል። በዚህ ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ ትሆናለች በሚል ስትጠበቅ የነበረችው አትሌት ትዕግስት ግርማ ከውድድሩ ራሷን ማግለሏን ቀድማ አስታውቃለች። የኦቶዋ ማራቶን አሸናፊዋ ትዕግስት በውድድሩ ራሷን ለማግለሏ እንደ ምክንያት የተነሳውም በጥሩ ብቃት ላይ አለመሆኗ ነው። በዚም ምክንያት ፉክክሩ በሁለቱ ኢትዮጵያዊያን መካከል እንደሚሆን ነው የሚጠበቀው። ብሩክታይት ደገፋ እና በላይነሽ ኦልጂራም በቶሮንቶው ማራቶን በሴቶች መካከል በሚካሄደው ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ናቸው። እአአ የ2013 የዓለም ሻምፒዮና የ10ሺ ሜትር እንዲሁም በዚያው ዓመት በተካሄደው ሃገር አቋራጭ ሻምፒዮና የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤቷ በላይነሽ ውድድሩን በበላይነት ታጠናቅቃለች የሚል ቅድመ ግምትም አግኝታለች። አትሌቷ እአአ በ2012 የለንደን ማራቶን ሃገሯን ወክላ በተካፈለችበት ማራቶን\n2:21:53 የሆነ እና እስካሁንም የግሏ ፈጣን ሰዓት አስመዝግባለች። በዚህ ውድድር ሌላኛዋ ተፎካካሪ እና አሸናፊ የመሆን ዕድል እንዳላት ግምት የተሰጣት ብሩክታይት 2:23:28 የሆነ ፈጣን ሰዓት አላት። የአትሌቶቹ የግል ፈጣን ሰዓት በሁለት ደቂቃዎች የሚበላለጥ ይሁን እንጂ፤ በመካከላቸው ብርቱ ፉክክር እንደሚደረግ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በድረ ገጹ ጠቁሟል። ባለፈው ዓመት በተካሄደው የሂውስተን ማራቶን የተገናኙት ሁለቱ አትሌቶች በብሩክታይት ስድስት ሰከንዶች የበላይነት ነበር ፉክክራቸው የተጠናቀቀው። በአንድ ቡድን ውስጥ የታቀፉት አትሌቶቹ የጋራ ስልጠና ከሌላቸው በቀር አንድ ላይ እንደማይለማመዱም ነው በላይነሽ የገለጸችው። አትሌቷ ከድረገጹ ጋር በነበራት ቆይታ፤ «እኔ ቡድኑን የተቀላቀልኩት በቅርቡ ስለሆነ ጓደኛሞች አልሆንም። በሂውስተን ስንገናኝ ግን ተግባቢ ሰው መሆኗን ተረድቻለሁ፤ ስለዚህ ወደፊት ጓደኛሞች እንደምንሆን እገምታለሁ» ብላለች። አትሌቶቹ በአሰልጣኝ ገመዱ ደደፎ በሳምንት ለሁለት እና ሶስት ጊዜያት በሰንዳፋ የሚሰለጥኑ ቢሆንም፤ እንዲህ ዓይነቱ አለመግባባት ያልተለመደ እና ከፉክክር ስሜት የሚመነጭ እንደሆነም ነው በዘገባው የተጠቆመው። በዚህ ዓመት የሂውስተን ግማሽ ማራቶንን 1:02:09 በሆነ ሰዓት የገባችው ብሩክታይት በበኩሏ ውድድሩን በጥሩ ሰዓትና በአሸናፊነት ለማጠናቀቅ ማለሟን ነው የገለጸችው።አዲስ ዘመን መስከረም 5/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "f42e879c28c33df6d489395af37e2811" }, { "passage": "ቦጋለ አበበበኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ወረርሽኙ መፍትሄ ባያገኝም እንደሚካሄድ እርግጠኛ የሚያደርጉ ማሳያዎችን አዘጋጆቹ ይፋ ሲያደርጉ ሰንብተዋል፡፡ ይሁን እንጂ በውድድሮች ለመሳተፍ ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ አትሌቶችና የስፖርት ቤተሰቦች ከወረርሽኙ ስጋት ጋር በተያያዘ ማሟላት ስለሚጠበቅባቸው መስፈርቶች ወጥ የሆነ ህግ በማውጣት ረገድ አዘጋጆቹ ለረጅም ጊዜ እንደተቸገሩ ይታወቃል፡፡ ይህም የቶኪዮ ኦሊምፒክ የመሰረዝ እድል ይገጥመዋል የሚል ስጋት በብዙዎች ዘንድ አሳድሮ ነበረ፤ይሁንና አዘጋጆቹ ከወረርሽኙ ስጋት ጋር በተያያዘ ተቸግረውበት የነበረውን ህግ ሰሞኑን ይፋ ማድረጋቸው ታውቋል፡፡ ወራትን ከፈጀ ምክክር በኋላ ሃምሳ አራት ገፅ የያዘ ሪፖርት ይፋ ያደረጉት የኦሊምፒኩ አዘጋጆች ወረርሽኙ በቀጣይ ሰባት ወራት ውስጥ መፍትሄ ባያገኝ እንኳን ኦሊምፒኩ መካሄድ የሚችልባቸውን ከጤና ጋር የተያያዙ ሕግና ደንቦች ይፋ አድርገዋል፡፡ በዚህም አትሌቶችም ይሁኑ ተሳታፊዎች መደበኛ የኮቪድ-19 ምርመራ ማድረጋቸው እንደማይቀር ያስቀመጡ ሲሆን፣ ከወረርሽኙ ስጋት ጋር በተያያዘ የሚቀመጡ ገደቦችን የጣሰ ማንኛውም አትሌት የሚቀጣበትን ሕግ እንዳረቀቁ አስታውቀዋል፡፡ ውድድሩን ለመከታተል ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ የስፖርት ቤተሰቦች ለይቶ የማቆያ ጉዳይ እንደሚመለከታቸው የተገለፀ ሲሆን፣ ወረርሽኙን ለመከላከል ከሚያስፈልጉ የጥንቃቄ ርምጃዎች መካከል የአፍ ጭንብል ማጥለቅና አለመጨባበጥን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚገደዱም ተጠቁሟል፡፡ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዝግጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ጥብቅ የመከላከል ርምጃዎች ተግባራዊ እንደሚሆኑ ጠቁመው፣ ይህ የኦሊምፒኩን ድባብ የተለየ ቢያደርገውም በደማቅ ሁኔታ እንደሚከናወን ያላቸውን እምነት ለመገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል፡፡ ከየትኛውም አገር ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ አትሌቶች ጃፓን እንደደረሱ የኮቪድ-19 ምርመራ ይደረግላቸዋል፤ በኦሊምፒክ መንደር በሚኖራቸው ቆይታም በአራት ወይም አምስት ቀናት ልዩነት ተመሳሳይ ምርመራ ይደረግላቸዋል፡፡ በተለያዩ ምርመራዎች ወረርሽኙ የሚገኝባቸውን አትሌቶች በተመለከተም የማገገሚያ ማዕከል እንደሚኖር ተጠቁሟል፡፡ ይሁን እንጂ አትሌቶች በውድድር ወቅት በወረርሽኙ ቢጠቁ የውድድር ሕጎች ላይ ስለሚያሳድረው ተፅዕኖ የተገለፀ ነገር የለም፡፡ አትሌቶች ከውድድርና ልምምድ ውጪ የአፍ መሸፈኛ ጭምብል የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ተጠቁሟል፤ ድምፅን ከፍ አድርጎ ማውራትና ከሌሎች ጋር ንኪኪ መፍጠር እንደማይችሉ ተገልጿል፡፡ ለዚህም እያንዳንዳቸው በቅድሚያ ለነዚህ ሕጎች ተገዢ እንደሆኑ የሚያረጋግጡበት የስነምግባር ደንብ እንደሚፈርሙ ታውቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሁሉም አገራት የስፖርት ልዑካን ቡድኖች ውድድሮቻቸውን እንዳጠናቀቁ በፍጥነት አገሪቱን ለቀው መውጣት እንዳለባቸውና ውድድሮች ከተጠናቀቁ በኋላ ለጉብኝት ወይም ለሽርሽር ተጨማሪ ቀናትን በጃፓን መቆየት እንደማይቻል ተገልጿል፡፡ የተቀመጡትን ሕግና ደንቦች ጥሰው የተገኙ አትሌቶች ወይም የስፖርት ቤተሰቦች ምን አይነት ቅጣት እንደሚጠብቃቸው እስካሁን የተቀመጠ ነገር ባይኖርም አዘጋጆቹ ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጋር በዚህ ጉዳይ ላይ እየሰራ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ የተቀመጡት ደንቦች ስፖርት መዝናኛ እንደመሆኑ በመጠኑም ቢሆን የማስጨነቅ ባህሪ እንዳላቸው ቢታመንም ሕጎቹን እንደ ወንጀል መቅጫ ሕግ መመልከት ሳይሆን ለጥንቃቄ ሲባል የተወሰዱ እንደሆኑ መገንዘብ አስፈላጊ እንደሚሆን አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ ሕግና ደንቦቹን አትሌቶችና ልዑካን ቡድኖች በአግባቡ እንዲገነዘቡ በቡድን መሪዎች በኩል የተለያዩ ማብራሪያዎችና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ይፈጠራሉ፤ስቴድየም ገብተው ውድድሮችን የሚመለከቱ የስፖርት ቤተሰቦችን ቁጥር ለመወሰን ወቅቱ ሲደርስ የወረርሽኙ ስርጭት በዓለም ላይ የሚኖረውን ነባራዊ ሁኔታ መጠበቅ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል፡፡ በኦሊምፒኩ ለመታደም ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ የስፖርት ቤተሰቦች ለሁለት ሳምንታት በለይቶ ማቆያ እንዲቀመጡ ማድረግ እንደማይቻል የገለፁት አዘጋጆቹ፣ ሌሎች አማራጮችን እንደሚጠቀሙ ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ የወረርሽኙ ክትባት እንደተገኘና በርካታ አገራትም በግዢ ሂደት ላይ እየተረባረቡ መሆኑ እየተሰማ ቢሆንም፣ ኦሊምፒኩ እስከሚካሄድበት ወቅት ድረስ ለዓለም ሕዝብ ሊዳረስ ስለማይችል የኦሊምፒኩ አዘጋጆች አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ ውድድሩን በታሰበው ጊዜ ማካሄድ የግድ እንደሆነ አምነው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ የወረርሽኙን ስጋት ለመቅረፍ በሚደረጉ የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎች የኦሊምፒክ አዘጋጆች ምን ያህል ወጪ እንደሚጠብቃቸው ቁርጥ ያለ መረጃ ባይኖርም፣ ባለፈው ሳምንት የወጡ ሪፖርቶች እስከ አንድ ቢሊየን ዶላር ሊፈጅ እንደሚችል አመላክተዋል፡፡ ኦሊምፒኩን በታቀደው ጊዜ ማካሄድ ካልተቻለና የመራዘም እድል ከገጠመው ደግሞ አዘጋጆቹ ቀደም ብለው ከያዙት በጀት እስከ ሁለት ቢሊየን ዶላር ድረስ ተጨማሪ ወጪ ሊያወጡ እንደሚችሉ በቅርብ የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 30/2013", "passage_id": "59e014c49aaf9951044da734cee2ec85" }, { "passage": "በመቀጠልም ከሁለት ወር በኋላ በሮም ማራቶን አሸናፊ ሆነች። ከሮም አሸናፊነት በኋላም በ1996 በአትላንታ አሜሪካ በሚደረገው የኦሊምፒክ ውድድር በ2:26:05 በሆነ ሰዓት አንደኛ በመሆን አጠናቀቀች። \n\nበወቅቱ ፋጡማን በመከተል ሁለት ደቂቃ ዘግይተው የሩሲያዋ ቫለንቲና ይጎሮቫና ጃፓናዊቷ ዩኩ አርሞሪ 2ኛና 3ኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል። \n\nከ1997 እስከ 1999 የተካሄዱ የቦስተን ማራቶን ውድድሮች በተከታታይ ያሸነፈችውን ፋጡማ የ'ቦስተኗ ንግሥት' የሚል ቅጽል ስም አግኝታበታለች።\n\nለአትሌት አበበ ቢቂላ ትልቅ ፍቅር እንደላት የምትናገረው አትሌት ፋጡማ ሮባ \"አቤን በደንብ እወደዋለሁ፤ አደንቀዋለሁ። አቤን እኔ ብቻ ሳልሆን መላው ዓለም ያደንቀዋል\" ትላለች።\n\nለዓመታት ከአገርና ከአትሌቲክሱ መድረክ ርቃ የቆችው የኦሊምፒኳ ኮከብ አትሌት ፋጡማ ከቢቢሲ ጋር ባደረገችው ቆይታ ስለ ህይወቷ እንዲህ ብላለች። [የተጠቀሱት ዓመታት በሙሉ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ናቸው]\n\nስለ አትሌቲክስ ምንም የማውቀው ነገር የለኝም\n\nበ1970 ዓ.ም በአርሲ ዞን ሌሙና ቢልቢሎ ወረዳ፣ ሁሉሌ ካራ በሚባል ስፍራ ተወለድኩ። ገጠር ውስጥ ከአርሶ አደር ቤተሰብ ነው የወጣሁት። ኑሮዬና ትምህርቴም እንደ ማንኛውም የገጠር ልጅ ነበር።\n\nበገጠር እንዳደጉት ልጆች ከብቶችን ስጠብቅና ቤተሰብን ስረዳ ስለቆየሁ ቶሎ ትምህርት ቤት አልገባሁም። ትምህርት ቤቱም ከቤተሰቤ ርቆ ስለሚገኝ በደንብ ካደግሁ በኋላ በደርሶ መልስ 14 ኪሎ ሜትር በእግር ተጉዤ እማር ነበር።\n\nያደግኩበት ገጠር ቴሌቪዥንም ሆነ ሬዲዮ አልነበረም።\n\nስለዚህ ስለአትሌቲከስ የማውቀው ነገር አልነበረም። ይሁን እንጂ በትምህርት ቤት ውስጥ እኣወዳደሩ ነጥብ ይይዙልን ነበር።\n\nአስተማሪያችን መሃረብ ይዞልን \"ማን ቀድሞ ይነካል\" እያለ ያወዳድረን ነበር። \n\nእኔ ከሴቶች ጋር ተወዳድሬ አሸንፋለሁ። ወንዶችንም ቢያመጡ አሸንፍ ነበር። ከዚያ በኋላ ከትምህርት ቤቴ ተመርጬ በወቅቱ አውራጃ ወደሚባለው፣ ከዚያ ደግሞ ክፍለ አገር ለሚባለው ተወክዬ መወዳደር ጀመርኩኝ። በዚሁ ነው እንግዲህ ወደ አዲስ አበባ መጥቼ የተለያዩ የስፖርት ቡድኖች መኖራቸውን ያወቅኩት።\n\nክፍለ አገርን ወክዬ በተወዳደርኩበት ጊዜ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ቡድን አይቶኝ ሃጂ ቡልቡላ የሚባለል ሰው ላከብኝ።\n\nእርሱም ቡድኑ እንደሚፈልገኝ፣ ትምህርቴንም እንድማር፣ ደሞዝም እንደሚከፍሉኝ ነገረኝ።\n\nእኔም ቤተሰቤን ሳማክር ብዙም ደስተኛ ስላልነበሩ ሊከለክሉኝ አሰቡ። ይሁን እንጂ ሃጂን ካዩ በኋላ ፈቀዱልኝ፤ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ መጣሁ።\n\nተስፋ መቁረጥና ወደ ስኬት ጉዞ\n\nበ1994 እኤአ ቤልጂየም አገር ነበርኩኝ። እዚያም በአገር አጭር ውድድሮች ላይ በመሮጥ ተሳተፍኩኝ።\n\nቤልጂየም በቆሁበት ወቅት አንድ ማራቶን የምትሮጥ ሴትን በፓሪስ ማራቶን ለምን ካንቺ ጋር አልሮጥም ብዬ ጠየቅኳት።\n\nእርሷም ነይ አብረን እንሂድ አለችኝ። ከዚያም በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1994 በተካሄደው የፓሪስ ማራቶን ሳልዘጋጅ ተወዳደርኩ።\n\nውድድሩ ሲጀመር ከሌሎች አትሌቶች ጋር መሮጥ አቃተኝ። ጥለውኝ ሄዱ፤ ይሁን እንጂ ወደ 35ኛው ኪሎ ሜትር ላይ ደረስኩባቸው።\n\nከእነርሱ ጋር ግን መቀጠል አልቻልኩም ጥለውኝ ሄዱ። በጣም ደክሞኝ ስለነበር ውሃ ጠጣሁ። ውሃውም ሆዴን ወጥሮ ያዘኝ።\n\nውድድሩንም ብጨርስም ሁለተኛ አልሮጥም ብዬ ነበር።\n\nወደ አገር ቤት ስመለስ ግን ዶ/ር ወልደ መስቀል ኮስትሬ ማራቶን እንድሮጥ ጠየቁኝ።\n\nከዚያ በኋላ ስልጠና ወስጄ እንዴት ማራቶን እንደምሮጥ ተማርኩ። ወደ ሞሮኮ ሄጄም ማራካሽ ላይ ማራቶን ተወዳደርኩ።\n\nከሞሮኮ ሞሮኮሽ እስከ ቦስተን\n\nበ1996 የማራካሽ ማራቶን ላይ ብዙም ስልጠናና ልምምድ ሳላደርግ ነበር... ", "passage_id": "fcb849fe6b606c522e8877edaf43d96a" }, { "passage": "በቻይና ከወር በፊት የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እየተፈጠረ እንደሚገኝ ተደጋግሞ ተነግሯል፡፡ ይህ ገዳይ ወረርሽኝ በዓለም ስፖርት እንቅስቃሴ ላይ ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተጋኖ አይነገር እንጂ በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ኩነቶች ላይ ካሳደረው ተፅዕኖ የባሰ እንጂ ያነሰ እንዳልሆነ በርካታ ማሳያዎች መውጣት ጀምረዋል፡፡ በእርግጥ በዚህ ቫይረስ ምክኒያት ቻይናን ጨምሮ በበርካታ አገራት ዓለማቀፋዊ ውድድሮች የተሰረዙ ቢሆንም የዓለም ህዝብ ትኩረት ከአምስት ወር በኋላ በቶኪዮ የሚካሄደው የ2020 ኦሊምፒክ ላይ ነው፡፡ የኦሊምፒክ ውድድሩን በበላይነት የሚመሩት አካላት ግን ታላቁን የስፖርት መድረክ መሰረዝ ወይም የሚካሄድበትን ጊዜ ማራዘም የማይታሰብ መሆኑን ከሳምንታት በፊት ሲናገሩ ነበር፡፡ በቫይረሱ ስጋት ምክኒያት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ምንም አይነት አደጋ እንዳላንዣበበት አፅኖት ሰጥተው መግለጫ ሲያወጡም ከርመዋል፡፡ ይሁን እንጂ የቫይረሱ ስርጭት ከመቀነስ ይልቅ በበርካታ አገራት እየተስፋፋ መሄዱን ተከትሎ የኦሊምፒክ አዘጋጆቹ ስጋት ውስጥ እንደገቡ የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣት ጀምረዋል፡፡ የቀድሞው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዚዳንት ዲክ\nፖንድ በኮሮና ቫይረስ ስጋት የቶኪዮ ኦሊምፒክ በተያዘለት ጊዜ እንደሚካሄድ እርግጠኛ ሆኖ ለመወሰን ዓለም አቀፍ ኮሚቴው እስከ መጪው\nሰኔ ድረስ እንደሚታገስ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ አሁንም ድረስ የኮሚቴው አባል የሆኑት የቀድሞ የውሃ ዋና ተወዳዳሪ ፖንድ በቫይረሱ\nሳቢያ ብዙ መጥፎ ነገሮች እየተፈጠሩ እንደሚገኙ በማስታወስ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ውድድሩ ሁለት ወር እስኪቀረው ድረስ ስጋት እንደማይኖርበትና\nአስፈላጊው ነገር ሁሉ መሟላቱን ማረጋገጥ እንዳለበት ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ተናግረዋል፡፡ ከዚያ በኋላም ቶኪዮ ውድድሩን እንደምታካሂድ\nወይም እንደሚሰረዝ፣ ካልሆነም እንደሚራዘም ውሳኔ ላይ መድረስ እንደሚቻል ፖንድ ገልፀዋል፡፡ ከሳምንት በፊት የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ ከጃፓናዊቷ የሜዳ ቴኒስ ኮከብ ተጫዋች ናኦሚ ኦሳካ ጋር በመሆን\n‹‹በስሜት አንድ እንሁን›› የሚለውን የውድድሩን መሪ ቃል በተንቀሳቃሽ ምስል ለዓለም ሲያስተዋውቁ ታይተዋል፡፡ በዚህ ወቅት የዓለምን\nህዝብ በስሜት አንድ ያደረገው ጉዳይ ግን ከኦሊምፒኩ ይልቅ የኮሮና ቫይረስ ስለመሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡ የቅርብ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት\nበኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በዓለም ዙሪያ 75 ሺ ሰዎች ተጠቅተዋል፡፡ ከሁለት ሺ በላይ ሰዎች በዚሁ ቫይረስ ሳቢያ ሕይወታቸው ያለፈም\nሲሆን ቫይረሱ በሃምሳ የዓለም አገራት ተሰራጭቷል፡፡ የዚሁ ወረርሽኝ መነሻና ክፉኛ ተጎጂ የሆነችው ቻይና ፕሬዚዳንት ዢ ጂፒንግ\n‹‹ሰይጣኑ ቫይረስ›› ብለው እንደጠሩት ሁሉ የቫይረሱ ስርጭት በአስደንጋጭ ሁኔታ እየተስፋፋ የዓለም ተመራማሪዎችም ፈውሱን የማግኘት\nጥረት ተጨባጭ ተስፋ እንዳላመጣ እየተስተዋለ ይገኛል፡፡ ይህም የዓለምን ምጣኔ ሀብት በተያዘው 2020 ሩብ ዓመት ብቻ 280 ቢሊየን ዶላር ኪሳራ እንደሚያደርስ በጥናት\nተጠቁሟል፡፡ ይህም እ.ኤ.አ ከ2009 ወዲህ የመጀመሪያ ይሆናል፡፡ በቫይረሱ ስርጭት ከቻይና ቀጥላ በሁለተኛነት የተቀመጠችው ጃፓን\nውስጥ ከሰባት መቶ ያላነሰ ሰው በቫይረሱ መጠቃቱ ተዘግቧል፡፡ የቅርብ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ግን 3700 ሰዎች በቫይረሱ መጠቃታቸውንና\nየኦሊምፒክ ውድድሩ ከሚካሄድባቸው አካባቢዎች ዋነኛ ከሆነው ዮኮሃማ ቤዝ ቦል ስቴድየም ከሦስት ኪሎ ሜትር ባነሰ ርቀት ላይ በሚገኝ\nስፍራ ላይ በመገለል እንደተቀመጡ ታውቋል፡፡ ይሁን እንጂ ጃፓን በቀጣዩ ወር በአርባ ሰባት ግዛቶቿ ለ121 ቀናት የሚዞረውን የኦሊምፒክ\nችቦ ለመለኮስ ተዘጋጅታለች፡፡ የኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴው መሪ ቶሺሮ ሙቶ የኦሊምፒክ ውድድሩን ለማስተናገድ ምንም ስጋት እንደሌለ\nቀደም ብለው ቢፎክሩም አሁን አሁን ስጋት ውስጥ እንደገቡ በግልፅ በአገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው ተናግረዋል፡፡ በግልፅ የቫይረሱ ስጋት\nውድድሩን ያስቀረዋል ባይሉም በኦሊምፒኩ የሞቀ ዝግጅት ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ሊከልስ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልፀዋል፡፡ በቫይረሱ ስጋት የተነሳ ቶኪዮ የኦሊምፒክ ውድድሩን የመሰረዝ አዝማሚያ ባይታይባትም ባለፈው ሳምንት በተካሄደው\nየቶኪዮ ማራቶን ከአትሌቶች በስተቀር ሕዝብ እንዳይሳተፍ አድርጋለች፡፡ ከሁለት ቀናት በፊትም የጃፓን የኦሊምፒክ ሚኒስትሯ ሴኮ ሃሺማቶ\nበአገሪቱ ፓርላማ በጉዳዩ ዙሪያ በቀረበላቸው ጥያቄ ማብራሪያ ሲሰጡ፣ ቶኪዮ ውድድሩን በ2020 ለማካሄድ ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ\nኮሚቴ ጋር ውል እንደገባ በማስታወስ በውሉ መሰረት ውድድሩን እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ የማራዘም እድል እንዳለ አስረድተዋል፡፡\nይሁን እንጂ ውድድሩ በተያዘለት ጊዜ እንዲካሄድ የተቻለውን ሁሉ ለማድረግ እየተሞከረ መሆኑን ሚኒስትሯ አብራርተዋል፡፡የኦሊምፒኩ አዘጋጅ ኮሚቴ ውድድሩን ለማካሄድ የልብ ልብ የተሰማቸው ወቅቱ በጋ እና ከፍተኛ ሙቀት የሚኖርበት\nከመሆኑ ጋር ተያይዞ የኮሮና ቫይረስ ልክ እኤአ 2003 ላይ የሳርስ ወረርሽኝ በበጋ ወራት ሊጠፋ እንደሚችል ተስፋ አድርገው መሆኑን\nመረጃዎች ወጥተዋል፡፡ ይሁን እንጂ የሳርስ ወረርሽ ለምን በበጋ ወራት እንደሚጠፋ አሁንም ድረስ በህክምናው ዓለም ግልፅ ማስረጃ እንደሌለ የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ በሚኒሶታ ዩኒቨርስቲ የህክምና\nተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ሚካኤል ኦስተርሆልም አንዳንድ የኮሮና ቫይረስ አይነቶች ከክረምት ወራት ይልቅ በበጋ እንደሚስፋፉ በመጠቆም\nየኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴው ባዶ ተስፋ መሆኑን ከታይም መፅሔት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አረጋግጠዋል፡፡ ጃፓን ለዓመታት የለፋችበት የኦሊምፒክ ዝግጅት ከንቱ ከሚቀርና\nቫይረሱ ይዞ ከሚመጣው አደጋ አንዱን መምረጥ ያለባት ወቅት ላይ ትገኛለች፡፡ የኦሊምፒክ ውድድሩ ቢሰረዝ ወይም የቦታ ለውጥ ቢደረግበት\nጃፓን የሚገጥማትን ኪሳራ ያሰሉ የምጣኔ ሀብት ምሁራን ቀላል እንዳልሆነ ይናገራሉ፡፡ ለውድድሩ 25 ቢሊየን ዶላር ወጪ እንደሚሆን\nየታሰበ ሲሆን የመሰረዝ ወይም የቦታ ለውጥ የሚደረግበት ከሆነ ቀድሞ ከታሰበው በአራት እጥፍ ሊያስወጣ እንደሚችል ቢቢሲ ሰሞኑን\nባስነበበው ዘገባ አትቷል፡፡ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ በዘለቀው የዘመናዊው ኦሊምፒክ ታሪክ ታላቁ የስፖርት መድረክ በጦርነት ካልሆነ\nበስተቀር በሌላ ምክኒያት ተራዝሞ ወይም ተሰርዞ አያውቅም፡፡ ነገር ግን ኦሊምፒክ የአሁኑን ያህል ከባድ ፈተና ገጥሞት ያውቃል ለማለትም\nአይቻልም፡፡አዲስ ዘመን አርብ የካቲት 27/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "3b406149853ba1ba565927d02432214e" }, { "passage": " በስፖርት የመጨረሻውን ደረጃ ክብር የሚያስገኘው ውድድር ኦሊምፒክ መሆኑ ይታወቃል። በዓለም ትልልቅ ስም ያላቸው ዝነኛ አትሌቶች ሃገራቸውን ወክለው የሚሳተፉበት እንዲሁም በርካታ ክብረወሰኖች የሚሰባበሩበትም ነው። በመሆኑም በአትሌቶች ዘንድ በመድረኩ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ብቻም ሳይሆን ተሳትፎውም ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው።ኦሊምፒክ በየአራት ዓመቱ ስለሚካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት የሚደረግበት ሲሆን፤ ወጥ አቋም የሌላቸው አትሌቶች በተደጋጋሚ ኦሊምፒክ ላይ ሊታዩ አይችሉም። በመሆኑም በርካታ ተሳትፎ ያላቸው አትሌቶችን ለማግኘት አዳጋች ነው። እንግሊዛዊቷ አትሌት ግን በመጪው ዓመት ስድስተኛ የኦሊምፒክ ተሳትፎዋን ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኗን ነው ያሳወቀችው። በተለይ ለወጣት አትሌቶች አስተማሪ የሆነ ተሞክሮዋንም ለቢቢሲ አጋርታለች።ጆ ፓቬ አምስት አሊምፒኮች ላይ የተሳተፈች አንጋፋ አትሌት ስትሆን በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስድስተኛ ተሳትፎዋን በማድረግ የክብረወሰን ባለቤት ለመሆን ፍላጎት አላት። ከዚህ ቀደም የሃገሯ ልጅ የሆነችው ጦር ወርዋሪ ቴሳ ሳንደርሰን ስድስት ኦሊምፒኮች ላይ ሀገሯን የወከለች አትሌት በመባል ተመዝግባለች። ፓቬ ስድስተኛዋን ተሳትፎ የምታደርግ ከሆነ ደግሞ በመም አትሌት የመጀመሪያዋ ትሆናለች።\nፓቬ እአአ በ2014 ከወሊድ በኋላ በአውሮፓ ሻምፒዮና በ10ሺ ሜትር ስትሳተፍ በአንጋፋነቷ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆና ነበር። ይሁን እንጂ በ40ዓመቷ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆን ብቃቷን ማስመስከር ችላለች። በቶኪዮው ኦሊምፒክ ስትሳተፍም ዕድሜዋ 46 ስለሚሆን ምናልባትም በኦሊምፒኩ አንጋፋዋ አትሌት ልትሆን ትችላለች። ፓቬ ለቢቢሲ በሰጠችው አስተያየት ላይም «ዕድሜዬን ረስቼ ስድስተኛውን የኦሊምፒክ ተሳትፎዬን አደርጋለሁ» ብላለች።አትሌቷ ሃገሯን ወክላ በኦሊምፒክ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው እአአ በ2ሺ በተካሄደው የሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ ነበር። «በቶኪዮ የሚካፈለው ብሄራዊ ቡድን ጥሩ ተፎካካሪ እንዲሆን እፈል ጋለሁ። በመሆኑም ዝግጅታችንን ቀድመን መጀመር ይገባናል፤ ፉክክሩ ደግሞ ይበልጥ ደስ የሚያሰኝ ነው» ብላለች። የሁለት ልጆች እናት የሆነችው አትሌቷ ከኦሊምፒኩ አስቀድሞ በዘንድሮው የዶሃ ዓለም ሻምፒዮና አቅሟን የመፈተሽ ፍላጎት እንዳላትም ጨምራ ገልጻለች። እአአ በ2017 በለንደን በተካሄዱት ሁለት ትልልቅ የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ ብትሆንም አልተሳካላትም ነበር። በለንደን ማራቶን ውድድሯን ሳታጠናቅቅ አጋማሽ ላይ ስታቋርጥ፤ በ10ሺ ሜትር በተካፈለችበት ሻምፒዮና ደግሞ በጉዳት ምክንያት ውድድሯን ለማጠናቀቅ አልቻለችም ነበር።ያለፈው ዓመት በተካሄደ ሌላ ውድድር ግን በረጅም ርቀት የመም ላይ ውድድር ሶስተኛ በመሆን የነሃስ ሜዳሊያውን ወስዳለች። በባለቤቷ የምትሰለጥነው አትሌቷ በልምምድ ቦታዎች ላይም ነፍስ ያላወቁ ልጆቿን ይዛ ትሄዳለች «ሩጫ እወዳለሁ፤ የአእምሮ እና ሰውነት ጤናን ለማግኘት ያግዛል። ከቤተሰብህ ጋር ሆነህ ስትከውን ደግሞ ይበልጥ መነሳሳትን ይፈጥራል። ባለቤቴ ያግዘኛል፤ ሥራችንን የምንሰራውም እንደ ቡድን ነው። ሯጭ ስትሆን መጨናነቅን ማስወገድ የግድ ነው ይህም የአእምሮን ጤና ይሰጣል። እድሜህንም እንደ ልምድ መጠቀም ትጀምራለህ» ስትልም የህይወት ልምዷን ታጋራለች።የአትሌቷ የኦሊምፒክ ተሳትፎ በተለያዩ ችግሮች የታጀበ ይሁን እንጂ ተስፋ አለመቁረጧ ግን ለብዙዎች ተሞክሮ የሚሆን ነው። እአአ 1997 ከባድ የሆነና ውስብስብ ቀዶ ጥገና የሚያስፈልገው የጉልበት ጉዳት የደረሰባት ቢሆንም፤ ከዚያ አገግማ በሲድኒ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። እአአ በ2004ቱ የአቴንስ ኦሊምፒክ ከመሳተፏ ሶስት ወራት በፊት የጡንቻ ጉዳት ቢደርስባትም አምስተኛ ደረጃ በመያዝ የዲፕሎማ ተሸላሚ ነበረች።በ2008ቱ የቤጂንግ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሯን ያጠናቀቀችው ደግሞ በውድድሩ ዋዜማ በምግብ መበከል የጤና መታወክ ስለደረሰባት ነበር። በሀገሯ በተዘጋጀው የ2012 ኦሊምፒክ በ5 እና 10ሺ ሜትር ውድድሮች ተሳትፎዋ ሰባተኛ ደረጃ በመያዝም የመጀመሪያዋ አውሮፓዊት አትሌት ተሰኝታለች። በሪዮ በተካሄደው የ2016ቱ ኦሊምፒክ ደግሞ ዘግይታ ውድድሩን በመጀመሯ በ10ሺ ሜትር 15ኛ ደረጃን ነበር የያዘችው። «የሪዮ ኦሊምፒክ ተሳትፎዬ በጣም አስደሳች ነበር፤ አብረውኝ የሮጡት አትሌቶችም ከእኔ በ20ዓመት የሚያንሱ ነበሩ። ቢሆንም ሁሌም ሃገሬን መወከል ለእኔ ኩራት ነው» ስትልም ትገልጻለች።አዲስ ዘመን ጥር 13/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "121a3477a1e1f36d985d4b50ab4afece" } ]
140f7f0aaf71057846ff7472b1a0bc11
c2c19c50dfe36b2204fac2582e0ac2fc
ስፖርቱ ስለምን ይሸበራል?!
እኤአ ታኅሣሥ 31 ቀን 2019 በቻይና ዉሃን ከተማ የኮሮና ቫይረስ መከሰቱን የዓለም የጤና ድርጅት ማስታወቁን ተከትሎ የቻይና መንግሥት በአፋጣኝ የቫይረሱን ስርጭት በአጭሩ ለመቅጨት እርምጃ ወደ መውሰድ ገብቶ ነበር። የቫይረሱን ስርጭት እንደተባለው በቀላሉ ለመቆጣጠር ሳይቻል ቀርቷል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭቱ ወረርሽኝ ደረጃ መድረሱን ተከትሎ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ አደጋ ጥሏል። የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ለውጦችን ከማስተናገድ አልፎ ቆሞ ቀር ለመሆን ተገዷል፡፡ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንም እስከ ትናንት በስቲያ ድረስ መካሄድ አለማኬዱ ያለየለት ቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ብቻ የዜና ግብዓታቸው የሆነ መስሏል፡፡ ዓለም በእንዲህ ዓይነት አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩን በተያዘለት ጊዜ ለማካሄድ ለረጅም ጊዜ ደረቅ አቋም መያዙ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል፡፡ የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣትና የአንድ ሀገር ስጋት ከመሆን ወደ ዓለም አቀፍ ስጋትነት እያደገ መምጣት ነገሮችን እንዲቀየሩ አድርጓል፡፡ በኦሊምፒክ መድረክ የሚሳተፍ አገራት «በመድረኩ እንሳተፍ» ወደሚል ውሳኔ ላይ እንዲደርሱም አድርጓል። የ2020 ኦሊምፒክ መካሄድ የለበትም የሚሉ ሀሳቦች ቀስ በቀስ መነሳታቸውም ውድድሩ ይራዘም የሚሉ ድምጾች ከቀን ወደ ቀን ብዛትና ጉልበት እንዲያገኙ አቅም ፈጥሮላቸዋል፡፡ የኦሊምፒክ መድረኩ የማይራዘም ከሆነ ስፖርተኞቻችንን ለአደጋ አናጋልጥም፣ ዓለም በጭንቅ ውስጥ እያለች ከሚካሄደው የ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ ይቅርብን ያሉ እንደ ካናዳ ያሉ አገራት ራሳቸውን እስከማግለል ደርሰዋል። የካናዳን እግር በመከተል እንደ አውስትራሊያ ያሉ አንዳንድ አገራት ተመሳሳይ ውሳኔ ላይ ደርሰዋል፡፡ የኢትዮጵያም የተሳትፎ ጉዳይ በአንድ ልብ ውሳኔ መስጠት ሳይቻል ቀርቶ ከፍተኛ ውዝግብ እስከማስነሳት የደረሰ ነበር። «የኢትዮጵያ አትሌቶች በውድድሩ ለመሳተፍ አንድ ላይ ሆቴል ገብተው ዝግጅት መጀመር አለባቸው የለባቸውም» በሚል በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መካከል ብርቱ የሆነ እሰጣ አገባ መፈጠሩ አይዘነጋም፡፡ ይሁን እንጂ የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከቀናት በፊት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ለአንድ ዓመት ማራዘሙን ተከትሎ በሁለቱ አካላት መካከል የነበረው የሃሳብ ልዩነት መቋጫ አግኝቷል፡፡ በኢትዮጵያ ስፖርት አመራሮች መካከል ሰሞነኛው ውዝግብ ዓለም አቀፉ ኮሚቴ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የረገበ ይምሰል እንጂ ነገ እንደ አዲስ አለመነሳቱን በርካቶች ይጠራጠሩታል፡፡ በሁለት ጎራ የተቧደኑ የስፖርት አመራሮች ውዝግብ ከየት ተነሳ?ብለን በመጠየቅ ወደ ኋላ መለሰ ብለን የተፈጠረውን ጉዳይ እንመርምር። ጥር 2 ቀን 2012 ዓ.ም. ቢሾፍቱ አዱላላ ሪዞርት፣የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዝግ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ጠርቷል። ወቅቱ ደግሞ የዓለም አገራት በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ የሚኖራቸውን ተሳትፎ በጎ መልክ ለማስያዝ ሽርጉድ እያሉ የሚገኙበት ነው። የኦሊምፒክ ኮሚቴ በዝግ ስብሰባ የቶኪዮ ኦሊምፒክን መሠረት ያደረገ ውሳኔን ይዞ ከመምጣት ይልቅ፤ «የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው የሥራ አመራር ቦርድ የአገልግሎት ዘመንና ተቋሙን በዋና ጸሐፊነት እንዲመራ፣ የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው የሥራ አመራር ቦርድ የቆይታ ጊዜ ከአራት ዓመት ወደ ስምንት ዓመት እንዲሻሻል ተደርጓል» የሚል ነበር። የኦሊምፒክ ኮሚቴ ይሄንኑ ውሳኔውን ተከትሎ ኮሚቴው ስፖርቱን ለማሳደግ የያዘውን ወንበር የሥልጣን ጊዜውን ለማሳደግ እየተውተረተረ መሆኑን አሳዛኝ እንደሆነ ከተለያዩ አካላት ትችቶች ሲሰነዘሩበት ነበር። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከዚህ ውስጥ አንዱ ሲሆን፤ ጉባዔው ውሳኔ ያሳለፈባቸው ጉዳዮች ተገቢነት ላይ ‹‹አልተስማማሁም›› ሲል ተቃውሞውን አሳውቋል፡፡ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የፌዴሬሽኑን ሀሳብ በመደገፍ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ሊታረም እንደሚገባ እስከ ማስገንዘብ ደርሶም ነበር። በዚህ መልክ የሚደረግ ሙግት ስፖርቱን መሠረት በማድረግ እንዲህ ዓይነት የሀሳብ ተቃርኖዎች የሚበረታቱ ቢሆንም፤ የስፖርቱ አመራሮች በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በመውጣት የሚሰጧቸው ምላሾችና የቃላት ልውውጦች ስፖርቱን መሠረት ያደረጉ አልነበሩም። በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ እና በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ በኩል በወቅቱ ይሰጧቸው በነበሩት ቃለ ምልልሶች ይሄንኑ በሚገባ የሚያንፀባርቁ ነበሩ። ስፖርቱን የሚመሩ ሌሎች አመራሮች የሚሰጡ አስተያየቶች ተመሳሳይ የነበሩ ሲሆን፤ ይህም ስፖርቱን መሠረት ያደረገ ቅራኔ አለመሆኑን በተጨባጭ መገንዘብ ያስችላል። ከስፖርቱ አመራሮች ውዝግብ ጀርባ ያለው ሴራ እንዳለ ሆኖ በክስተቱ ብዙዎችን ማስቆጣቱን የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነበር። የስፖርት አመራሮቹ ሲወዛገቡበት የነበረበት ወቅት ለቁጣው ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝግጅት ዙሪያ ከማተኮር ይልቅ፤ ባልተገባ ትርምስና ሽኩቻ ስፖርቱን ለመጥቀም ወይስ ለመጉዳት? ያስባለም ነበር። በዚህ ደረጃ ቅሬታን ካስነሳ በኋላ በሁለቱ ጎራ የነበረው ፀብ በይደር እንዲቆይ በማድረግ ተቋማቱ ትኩረታቸውን ወደ ኦሊምፒክ ለማድረግ ቃል ገብተው ነበር፡፡ ስፖርቱን የማሸበሩ ዜና ግን ዳግመኛ ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ተፈጥሯል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቶኪዮ 2020 አሊምፒክ ላይ ለሚደረገው ዝግጅትና ተሳትፎ በሚመለከት ባለድርሻ አካላትን ጋር ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ለዚህ እንደመነሻ ሆኗል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ‹‹በመድረኩ እንድንሳተፍ መልዕክት አልደረሰኝም›› ሲል ብሔራዊ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ትልቁን ባለድርሻ አካል ሳያሳትፍ የውይይት መድረክ መዘጋጀቱ ቅር መሰኘቱን አስታውቋል። አጋጣሚውም የሁለቱ ተቋማት ቁርሾ ለኦሊምፒክ እየተደረገ ያለው ዝግጅት በተናጠል እንዲሆን በር ከፍቷል፡፡ «በዝሆኖች ፀብ የሚጎዳው ሳሩ ነው» እንደሚባለው በስፖርቱ አመራሮች ሽኩቻ አገሪቷ ዋጋ እንዳትከፍል መፍትሄ መስጠት አስፈላጊ ቢሆንም በዝምታ ታልፏል፡፡ የአመራሮቹ ቁርሾ መፍትሄ አለማግኘቱን ተከትሎ መጋቢት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ ፤ የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በተያዘለት መርሐ ግብር መሠረት እንደሚካሄድ ገልጿል፡፡ በዚህ መሠረት አትሌቲክሱን ጨምሮ ለቶኪዮ 2020 የተመረጡ ብሔራዊ አትሌቶች ዝግጅት መጀመር እንዳለባቸው አስታወቀ። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ደግሞ ፤ «የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መፍትሔ ሳያገኝ ብሔራዊ አትሌቶችን በሆቴል አሰባስቦ ዝግጅት ማድረጉ አደጋ አለው» ሲል አስገነዘበ። ለብሔራዊ አትሌቶች የተደረገው ጥሪን ኃላፊነት የጎደለው እንደሆነ በመሞገት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ውሳኔ ፊት ለፊት ተጋፈጠ። የብሔራዊ ፌዴሬሽኑ አቋም እንደፀና የኦሊምፒክ ኮሚቴ ውሳኔው ተገቢና የማይቀለበስ መሆኑን አቋም በመያዝ ፍጥጫ ውስጥ ገቡ። በመጨረሻም ቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ እንዲሰረዝ የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ማስታወቁ ተከትሎ፤ በስፖርት አመራሮቹ መካከል የተፈጠረው ግብ ግብ ረገበ። ይህ ሽኩቻ እንዳለፉት ጊዜያቶች ተዳፈነ እንጂ አልጠፋም፡፡ ነገ እንደረመጥ የሚቆሰቁሰው አንድ አካል እንደሚኖር ሁለቱ አካላት አንዴ ሲሻኮቱ አንዴም ተስማማን እያሉ ውሃ ቢወቅጡት እንቦጭ እንደሚባለው መሆናቸውን ማስታወስ በቂ ነው፡፡ ለዚህም የሁለቱም ተቋሞች የበላይ የሆነው ስፖርት ኮሚሽን ኦሊምፒክ ሲመጣ ሳይሆን ከወዲሁ የሚስማሙበትን መንገድ መፈለግ እንዳለበት ይታመናል፡፡ በግለሰቦች ፍጥጫና የግል ፍላጎት ትልቁ የአገር ገፅታ ኦሊምፒክ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ የነገ ሳይሆን የዛሬ ጉዳይ ነው፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 18/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29263
[ { "passage": "በመላው ዓለም ከ210 ሀገራት በላይ የተዛመተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የዓለምን የስፖርት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ከቶታል። በወረርሽኙ ሳቢያ ትልልቅ የስፖርት ውድድሮች በመራዘማቸው፣ በመሰረዛቸው እና በመስተጓጐላቸው ኢንዱስትሪውን ከፍተኛ ገቢ እንደሚያሳጣው የተለያዩ ትንበያዎች አመልክተዋል። የስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰርሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል፡፡ በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በዚህ ዓመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል። \nየአብዛኛዎቹ የእግር ኳስ ክለቦች ዋነኛ ገቢያቸውን የሚያገኙት ከሶስት ምንጮች ሲሆን፤ ይኸውም ከመገናኛ ብዙሃን የስርጭት መብት፣ ከስፖንሰርና ማስታወቂያዎች እንዲሁም በጨዋታ ወቅት ከስታዲየም የትኬት ሽያጭ እንደሆነ የወርልድ ኢኮኖሚ ፎረም መረጃዎች ያመላክታሉ።10 በሚደርሱ ሊጎች ያለው ቁጥራዊ መረጃ እንደሚያሳየው ከሆነም ክለቦቹ ከሚዲያ መብት ብቻ ከ50 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያገኛሉ። ይህም ከአጠቃላይ ገቢያቸው 60 ከመቶ ይሸፍናል። በወረርሽኙ ምክንያት የውድድሮች መቋረጥን ተከትሎ ክለቦች ከእነዚህ ምንጮች የሚያስገቡት ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን ያመላክታል። \nዴይሊሜይል በዚሁ ዙሪያ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን እንደማሳያ በመጥቀስ ያወጣው ይሄንኑ ያጠናክራል። የዓለማችን እጅግ ተወዳጅ ከሆኑ ሊጎች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀሰው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በወረርሽኙ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳቱን በዘገባው ጠቅሷል። ፕሪምየር ሊጉ ባለፈው ዓመት አዲስ በገባው (ለሶስት ዓመታት) ኮንትራት 12 ቢሊዮን ዶላር ከሚዲያ መብት ብቻ ለመሰብሰብ አቅዶ ነበር። እግር ኳሱ አሁን ካለው ቁመና አኳያ እቅዱን ማሳካት የሚቻል አይሆንም ሲል ዘገባው አትቷል። \nውድድሩ ሁለት ወራትን እንኳን ሳያስቆጥር ክለቦቹ ከ60 እስከ 150 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ ማስተናገዳቸውን እያስታወቁ ይገኛሉ። በመሆኑም ከቴሌቪዥን መብት ከሚገኝ ገቢ ብቻ እያንዳንዱ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ክለብ 750 ሚሊዮን ፓውንድ ያጣል። ስለዚህ ፕሪሚየር ሊጉ በዚህ ምስቅል ቅል ውስጥ ሆኖ ለማግኘት ያቀደውን ገቢ ማሳካት እንደማይችል በመግለጽ ፤ የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የእግር ኳሱን ኢንዱስትሪ ለከፍተኛ የፋይናንስ ቀውስ የዳረገው መሆኑን በዘገባው አትቷል። የእግር ኳስ ጨዋታዎችና መሰል እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ መደረጉን ተከትሎ እንደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁሉ በሁሉም ሀገራት የሊግ ውድድሮች ላይ መጠኑ ይለያይ እንጂ በፋይናንስ ቀውሱ የተጎበኙ መሆናቸው መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። በተለይ በአህጉር አፍሪካ የሚገኙት ክለቦችና ብሄራዊ ፌዴሬሽኖችን በከፍተኛ ደረጃ እንዳቃወሳቸው ተነግሯል። የአፍሪካ ሀገራት ወረርሽኙን ለመከላከል የእንቅስቃሴ እግዳ መጣላቸውን ተከትሎ ኢኮኖሚያዊ መቃወስ ውስጥ አስገብቷቸዋል። የኢኮኖሚው መቃወስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የክለቦች ቀጣይ ህልውና አስጊ ደረጃ የሚያደርስ ይሆናል። በዓለም አቀፍ ደረጃ አንቱ የተባሉ የእግር ኳስ ተንታኞች «የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የዓለም እግር ኳስን በተለይ የአፍሪካ እግር ኳስን ከባድ ፈተና ይገጥመዋል» የሚሉ መላምቶችን እያስቀመጡ ይገኛሉ። የአህጉሪቱ እግር ኳስ በተለያዩ ችግሮች ተተብትቦ «የእድገት ውስንነት በሽታ» ሰለባ መሆኑን ያነሳሉ። የዓለም ፈተና የሆነው ኮቪድ-19 የወለዳቸው ችግሮች ተደምረውበታል። ይህም «በእንቅርት ላይ ጆሮ… » ያደርግበታል ። መጪው ጊዜ በተለይ ለአህጉር አፍሪካ እግር ኳስ ህልውና እጅጉን ፈታኝ እንደሚሆን መላምቶች እየተሰጡ ይገኛሉ። ለዓለም እግር ኳስ እድገትና ድምቀት እርሾ የሆነችውን አፍሪካ የእግር ኳኳ ህልውና ከገባበት አጣብቂኝ እንዲወጣ ድጎማ ማድረግ እንደሚገባ ምክረ ሃሳቦች ቀርበዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የቀረቡትን ምክረ ሃሳቦች መሰረት ያደረገ ተግባር ሊፈጽም መሆኑ በሳምንቱ መጨረሻ ይፋ አድርጓል። ካፍ ዓለምን በአንድ የጭንቀት ቀረጢት ውስጥ የከተተው የኮቪድ -19 ወረርሽኝ በእግር ኳሱ ላይ ያሳደረውን ጫና ከፍትኛ መሆኑን በመረዳት የበኩሉን ድጋፍ ለማድረግ ውጥን መያዙን አስታውቋል። \nኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ዓመታዊ የእግር ኳስ መርሐ ግብሮቻቸውን በዓለም አቀፉ ኮቪድ 19 ወረርሽን ምክንያት በሰረዙበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለአባል አገሮቹ የገንዘብ ድጎማ ሊያደርግ መሆኑ ታወቀ፡፡ ኮንፌዴሬሽኑ ለእያንዳንዱ አገር 200 ሺሕ ዶላር ሊሰጥ ማቀዱ ነው ያስታወቀው ፡፡የ54 አገሮች ብሔራዊ ፌዴሬሽኖችን የሚያስተዳድረው ካፍ፣ በየዓመቱ በመደበኛነት ከሚያከናውናቸው ውድድሮች መካከል የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግና የአፍሪካ ክለቦች ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ይሁንና ሁሉም በወረርሽኙ ምክንያት ውድድሮቹ እንዲሰረዙ አድርጓል፣ የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በሚመለከት አሁን ላይ ምንም ያለው ነገር የለም፡፡ \nየዘንድሮን የውድድር ዕጣ ፈንታ በሚመለከት ብዙዎቹ የአፍሪካ አገሮች ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ ስለመደረጉ ወይም ስለመሰረዙ ውሳኔ ላይ ባይደርሱም፣ 16 አገሮች መደበኛ ውድድሮቻቸውን መሰረዛቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ ኢትዮጵያ የዓመቱን ውድድር ከመሰረዟም በላይ በሚቀጥለው ዓመት በአፍሪካ የክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግና የክለቦች ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ውክልና እንደማይኖራት ለጊዜውም ቢሆን ይፋ አድርጋለች፡፡ የተቀሩት 15 አገሮች ደግሞ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ውድድሩ እስከተቋረጠበት ድረስ በደረጃ ሰንጠረዡ በተቀመጠላቸው ውጤት መሠረት የሚያሳትፏቸውን ክለቦች በማሳወቅ ውድድሮቻቸውን መሰረዛቸው ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ እነዚህም ቡርኪና ፋሶ፣ ጋምቢያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሞሪሸስ፣ አንጎላ፣ ኬቨርዴ፣ ጊኒ፣ ቶጎ፣ ዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ ኬንያ፣ ካሜሮን፣ ሩዋንዳ፣ ኒጀር፣ ኮንጎ ብራዛቪልና ላይቤሪያ ናቸው፡፡ \nበአጠቃላይ አህጉራዊው ተቋም እንደ አውሮፓና መሰል አህጉሮች በእሱ ሥር የሚያስተዳድረውን እግር ኳስ ወደ ገንዘብ በመለወጡ ረገድ ክፍተኛ ክፍተት ያለበት መሆኑ ተጠቅሷል ፡፡ ይሁንና ካፍ በየዓመቱ ለአባል አገሮቹ የሚሰጠውን የገንዘብ ድጎማ ሳያቋርጥ ለመስጠት ማረጋገጫ መስጠቱን የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የካፍን ድረ ገጽ ዋቢ በማድረግ ዘግበዋል፡፡ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለአባል ሀገራቱ የ200 ሺህ ዶላር ድጋፍ እንደሚያደርገው ሁሉ፤ የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) የ150 ሺህ ዶላር ድጋፍ አደርጋለው ማለቱን ይታወሳል። ከዓለም እግር ኳስ ራስ የሆነው ተቋም ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑ፤ ከሰሞኑ ደግሞ የአህጉሪቱ እግር ኳስ የበላይ ጠባቂ ካፍ ለአባል ሀገራቱ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል። የአፍሪካ እግር ኳስ በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ምክንያት መጪው ጊዜ ፈታኝ እንደመሆኑ፤ ፈተናውን በድጎማ ይታለፍ ይሆን?\nአዲስ ዘመን ግንቦት 25/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "2a7cf8fc16f8ee5a8efc81cc955ff885" }, { "passage": " እኤአ ታኅሣሥ 31 ቀን 2019 በቻይና ዉሃን ግዛት የኮሮና ቫይረስ እንደተከሰተ የዓለም የጤና ድርጅት ማስታወቁን ተከትሎ የቻይና መንግሥት በአፋጣኝ የቫይረሱን ስርጭት በአጭሩ ለመቅጨት እርምጃ ወደ መውሰድ ገብቶ ነበር። የቫይረሱን ስርጭት እንደተባለው በቀላሉ ለመቆጣጠር ሳይቻል ቀርቷል። አሁንም ቢሆን በዓለም አራቱም አቅጣጫዎች የተሰራጨውን ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ያስቻለ ፈውስ በዓለም ሳይንቲስቶች፣ የህክምና ጠቢባንም ይሁን በሀያላን አገራት አቅም ማምጣት አልተቻለም። ይህም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ከመለወጥ አንስቶ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በርካታ አሉታዊ ተፅዕኖው እንዲያርፍ አድርጓል፡፡ የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ተጽእኖ እያስተናገደ ከመሆኑ ባሻገር፤ ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጉን መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ የኮሮና ቫይረስ ለዓለም ራስ ምታት እንደሆነ በመቀጠሉ የስፖርቱ እንቅስቃሴ ዛሬም መፈተኑን ቀጥሏል። ስፖርታዊ ክንውኖች ለማድረግ አስቸጋሪ የመሆኑን ያህል በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ግምት ያለውን ኦሊምፒክ ጨዋታ እንዲራዘም ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ከሳምንት በፊት የ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ በምንም አይነት ሁኔታ ይካሄዳል የሚል አቋም የነበረ ቢሆንም በተቃራኒው ውሳኔ እንዲተላለፍ የቫይረሱ ስርጭት አስገድዷል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስፖርትን መፈተኑን እንደሚቀጥልም የቢቢሲ ዘገባ ያመለክታል። የዓለም ህዝብ የጋራ ስጋት በሆነው የኮቪድ -19 ወረርሽኝ በስፖርቱ ላይ እየደረሰ የሚገኘው ተጽእኖ እየጨመረ ይገኛል። በእንግሊዝ ዊምብልደን ላይ የሚደረገው እና የዓለማችንን ሥመጥር የሜዳ ቴኒስ ተጫዋቾች የሚያሳትፈው ታላቅ ውድድር እንዲሰረዝ ውሳኔ ተደርሷል። በዓለም ዓቀፍ ደረጃ እጅግ ተጠባቂ የሆነው ውድድር ለመሰረዙ የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ሆኗል። የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የስፖርቱን ገጽታን ምንኛ እየጎዳው እንደሚገኝ ይህ ትልቅ ማሳያ መሆኑንም ዘገባው ያትታል፡፡ ዘጋርዲያን ደግሞ፤ በእንግሊዝ ዊምብልደን ላይ የሚደረገው እና የዓለማችንን ሥመጥር የሜዳ ቴኒስ ተጫዋቾችን የሚያሳትፈው ውድድር ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተሰረዘ ጽፏል። የዊምብልደን ቻምፒዮና የተቋረጠው እኤአ ከ1940 እስከ 1935 ድረስ የዘለቀው የሁለተኛው ዓለም ጦርነት እንደነበር አስታውሷል። በዚህ ጦርነት መጨረሻ የአክሲስ ሃያላት ማለትም ጀርመን፣ ጣልያንና ጃፓን ተሸነፉ። እኤአ ታህሣሥ 2019 በተነሳው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት የ134ኛ ዊምብልደን ቻምፒዮና ተመሳሳይ እጣ ፈንታ ሊደርሰው እንደቻለ ዘገባው ተመልክቷል። የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ስፖርታዊ ክንውን ለማድረግ ፈታኝ እንደሆነው ሁሉ በአሁኑ ወቅት የኮሮና ቫይረስ የዓለምን ህዝብ እያሸበረ መሆኑን ተከትሎ ቻምፒዮናውን በተያዘለት መርሃ ግብር ለማካሄድ እንዳይቻል አድርጎታል።በዚሁ መሰረት ለሁለት ሳምንታት የሚካሄደው ይህ ስፖርታዊ ውድድር በሜዳ ቴኒስ ስፖርት አፍቃሪያንና ተወዳዳሪዎች ዘንድ ትልቅ ስፍራ ነበረው። ውድድሩ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው በሐምሌ ወር መጀመሪያ እንደነበር ታውቋል። በዩናይትድ ኪንግደም እስከ ሐምሌ ወር መጨረሻ ድረስ አንድም የቴኒስ ጨዋታ እንዳይካሄድም ውሳኔ ተላልፏል፡፡ ዘጋርዲያን 134ኛው የዊምብልደን ቴኒስ ቻምፒዮና መርሃ ግበር መሰረዙን ተከትሎ የዓለማችን እውቅ ተጫዋቾች ልብ እንደ ደማ ዘግቧል። የዊምብልደን የ8 ጊዜ ቻምፒዮናው ሮጀር ፌደረር ለዚህ ታላቅ መድረክ ባለፉት ሁለት ወራት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደረግ ነበር። ‹‹በቻምፒዮናው ላይ አዲስ ውጤት ለማስመዝገብ የነበረንን ተነሳሽነት ጨምሮ ሁሉም ነገር ተበላሽቷል» ሲል መከፋቱን ፌደረር ገልጿል። ሰሬና ዊሊያምስ በተመሳሳይ «የተሰማው ዜና እጅግ አስደንጋጭ ነው» ስትል የቻምፒዮናው መራዘም በስፖርቱ ቤተሰብ ላይ ሀዘን እንደፈጠረ ተናግራለች። ዶቼቬሌ በበኩሉ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት የስፖርቱን እንቅስቃሴና ገቢ ክፉኛ መጉዳቱን እንደቀጠለ ዘግቧል። ቶኪዮ-ጃፓን ሊደረግ ታቅዶ የነበረው የዘንድሮው ኦሊምፒክ በኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ወደ መጪው ዓመት እንደተራዘመው ሁሉ የዊምብልደን ውድድር መራዘሙ ትልቅ ሀዘን የፈጠረ ውሳኔ መሆኑን አመልክቷል። የቫይረሱን ስርጭት ተከትሎ በየአገሩ የተለያዩ የስፖርት ውድድሮች ተቋርጠዋል። ክለቦች፣ ተጫዋቾች፣ቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ የስፖርት ጋዜጠኞችና ሌሎችም ገቢ ማጣታቸውን እያስታወቁም ይገኛል። በዚህ ወቅት የዌምብልደን ቻምፒዮና መሰረዙ በስፖርቱ ላይ ተጨማሪ ድብርትን የሚፈጥር መሆኑን አመልክቷል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭቱ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን ተከትሎ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ አደጋ እየጣለ መምጣቱን ዛሬም መቀጠሉን ተከትሎ በስፖርቱ ዘርፍ ላይ የማይሻር ጠባሳ እንዲያርፍ ማድረጉን ዘግቧል። አዲስ ዘመን መጋቢት 25/2012 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "8f680d87be747024b1d0fe7df4aa9015" }, { "passage": "በመላው ዓለም ከ200 አገራት በላይ የተዛመተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የዓለምን የስፖርት እንቅስ ቃሴ በከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ከቶታል። በወረርሽኙ ሳቢያ ትልልቅ የስፖርት ውድድሮች በመራዘማቸው፣ በመሰረዛቸው እና በመስተጓጐላቸው ኢንዱስትሪውን ከፍተኛ ገቢ እንደሚያሳጣው የተለያዩ ትንበያዎች አመልክተዋል። የስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰ ርሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል፡፡በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል።በዚህ ዓመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል።የአብዛኛዎቹ የእግር ኳስ ክለቦች ዋነኛ ገቢያቸውን የሚያገኙት ከሶስት ምንጮች ሲሆን፤ ይኸውም ከመገናኛ ብዙሃን የስርጭት መብት፣ ከስፖንሰርና ማስታወቂያዎች እንዲሁም በጨዋታ ወቅት ከስታዲየም የትኬት ሽያጭ እንደሆነ የወርልድ ኢኮኖሚ ፎረም መረጃ ያመላክታሉ።10 በሚደርሱ ሊጎች ያለው ቁጥራዊ መረጃ እንደሚያሳየው ከሆነም ክለቦቹ ከሚዲያ መብት ብቻ ከ50 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያገኛሉ።ይህም ከአጠቃላይ ገቢያቸው 60 ከመቶ ይሸፍናል።በወረርሽኙ ምክንያት የውድድሮች መቋረጥን ተከትሎ ክለቦች ከእነዚህ ምንጮች የሚያስገቡት ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን ያመላክታል።ዴይሊሜይል በዚሁ ዙሪያ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን እንደ ማሳያ በመጥቀስ ያወጣው ይሄንኑ ያጠናክራል።የአለማችን እጅግ ተወዳጅ ከሆኑ ሊጎች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀሰው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በወረርሽኙ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳቱን በዘገባው ጠቅሷል። ፕሪምየር ሊጉ ባለፈው ዓመት አዲስ በገባው (ለሶስት ዓመታት) ኮንትራት 12 ቢሊየን ዶላር ከሚዲያ መብት ብቻ ለመሰብሰብ አቅዶ ነበር።እግር ኳሱ አሁን ካለው ቁመና አኳያ እቅዱን ማሳካት የሚቻል አይሆንም ሲል ዘገባው አትቷል።ውድድሩሁለት ወራትን እንኳን ሳያስቆጥር ክለቦቹ ከ60 እስከ 150 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ ማስተናገዳቸውን እያስታወቁ ይገኛሉ።በመሆኑም ከቴሌቪዥን መብት ከሚገኝ ገቢ ብቻ እያንዳንዱ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ክለብ 750 ሚሊዮን ፓውንድ ያጣል። ስለዚህም ነው ክለቦቹ ከተጫዋችና አሰልጣኞች ቡድን ባሻገር የሚገኙ ሰራተኞቻቸውን በጊዜያዊነት እያሰናበቱ ይገኛሉ ።የተጫዋቾቻቸውን ደመወዝ ለመክፈል በመቸገራቸውም አንዳንዶች ግማሽ ክፍያ ሌሎች ደግሞ የተወሰነ ቅናሽ በማድረግ እንደሚከፍሉ እያሳወቁ ይገኛሉ።ፕሪሚየር ሊጉ በዚህ ምስቅል ቅል ውስጥ ሆኖ ለማግኘት ያቀደውን ገቢ ማሳካት እንደማይችል ዴይሊ ሜል በዘገባው ተመልክቷል። በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ስፖርታዊ ክንውኖች መቆማቸው እንደ እንግሊዝና የመሳሰሉት ሊጎች ሁሉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ሰለባ መሆኑ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።ከብሄራዊ ፌዴሬሽኑ መግለጫ በመነሳት በአለማችን ታላላቅ ክለቦች ላይ የተከሰተው የፋይናንስ ቀውስ መንገዱና የኪሳራው መጠን ቢለይም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከችግሩ አለመዳኑን የዘርፍ ሙያተኞች እየተናገሩ ይገኛሉ።በፕሪሚየር ሊጉ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ክለቦች ከኮሮና ቀደም ብሎ በፋይናንስ ቀውስ የሚዋልሉ እንደሆኑ እሙን ነው። የተጫዋቾች ደመወዝ ለመክፈል የነበሩትን ውዝግቦች ወደ ኋላ መለስ ብለን ስናስታውስ ይሄንኑ እውነታ በሚገባ እንረዳለን።በክለቦቹ ላይ ከአስተዳደር፣ ከእቅድ፣ ገቢና ወጪን ያለማመጣጠን ችግሮች በስፋት የሚታዩ እንደሆነ የሚካድ አይደለም።ክለቦቹ ወጪን እንጂ ገቢን መሰረት ያደረገ የፋይናንስ ሥርአት የማይከተሉ በመሆኑ በቀውስ እንዲቆዩ ሆነዋል።የኮሮና ወረርሽኝ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚፈጥረው ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ሲታከልበት«በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ»ይሆናል።የወረርሽኙ ተፅእኖ ከክለቦች አልፎ የፌዴሬሽኖችን አቅም እየፈተነ ስለመሆኑ ከሰሞኑ የወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት የገንዘብ ችግር ውስጥ በመግባቱ መንግሥት የገንዘብ ድጎማ እንዲያደርግለት ጥያቄውን በደብዳቤ ማስገባቱን አስታውቋል፡፡የብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ እንዳብራሩት፣ «ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግለት ጥያቄ አቅርቧል መልስ እየጠበቀ ነው። ምክንያትም ሁሉም እንደሚያውቀው በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ሁሉም ነገር ቆሟል፣ የሁሉም አካላት ትኩረት ቅድሚያ ለሰው ልጆች ሕይወት በሚል ስፖርቱን በሚመለከት ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እያደረጉ እንዳልሆነ ይታወቃል። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ችግሩን መቋቋም በሚችልበት ቁመና ላይ አይደለም፣ ለዚህም ነው መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግ በደብዳቤ የጠየቅነው»ብለዋል።ሀገሪቱ ከገባችበት ፈተና አንፃር ብሄራዊ ፌዴሬሽኑን የመንግስትን ደጅ መጥናቱ ውጤትያመጣል የሚገመት አይሆንም ተብሏል።በተመሳሳይ የክለቦች እጣ ፈንታ ከዚህ የተለየ እንደማይሆን ከተለያዩ ወገኖች ግምቶች እየቀረቡ ይገኛሉ።ለዚህ እንደ መከራከሪያ በፕሪሚየር ሊጉ የሚሳተፍ አብዛኛዎቹ ክለቦች በመንግስት የሚደጎሙ መሆናቸውን ያነሳሉ። ሀገሪቱ እየገጠማት ካለው የኢኮኖሚ ቀውስ አንፃር መንግስት እንደቀደመው ለክለቦች ከፍተኛ ገንዘብ ስለማውጣቱ አጠራጣሪ ይሆናል ይላሉ።ከዚህ በመነሳት ክለቦችም ሆኑ ፌዴሬሽኑ ከነበረባቸው መጪውን ጊዜ ፈታኝ እንደሚሆንባቸው ሀሳባቸው እየሰነዘሩ ይገኛሉ። የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ከሰሞኑ ይፋ ያደረገው መረጃ ግን በኢትዮጵያን እግር ኳስ መፃኢ ጉዞ ላይ የተስፋ ጭላንጭል የፈጠረ ሆኗል። የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ፤«የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የፊፋ አባል አገራት ለሆኑት 211 ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች የ 150 ሚሊዮን ዶላር አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡በዚህ መሰረት እያንዳንዱ አባል ሀገራት ከሶስት ወራት በፊት የ500 ሺህ ዶላር ከፊፋ ድጋፍ ይደረግላቸዋል »ሲሉ አስታውቀዋል፡፡ፊፋ የሚያደርገው ድጋፍ የአለም እግር ኳስ ከገባበት ቀውስ ያወጣው ይሆን?የሚል ጥያቄ አጭሯል።በኢትዮጵያ ብቻም ሳይሆን በበርካታ ሀገራት በጉጉት የሚጠበቀው ገንዘብ ለማግኘት ፊፋ ቅድመ ሁኔታዎች ማስቀመጡም ተነግሯል።ሀገራት በወረርሽኙ ያደረሰባቸውን ተጽእኖ በተመለከተ በሚያቀርቡት ትንተና ላይ መሰረት ያደረገ ሊሆን ይችላልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይሄንኑ መሰረት ባደረገ መልኩ ተንትኖ ማቅረብ እንደሚጠበቅበት የዘርፍ ሙያተኞች እያሳሰቡ ይገኛሉ።ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ከክለቦቹ ጋር በሚገባ ተነጋግሮ የደረሰውን የጉዳትና የኪሳራ መጠን አስረጅና ገላጭ በሆነ መልኩ የሚያስረዳ ሰነድ መላክ ይኖርበታል።ብሄራዊ ፌዴሬሽኑም ሆነ ክለቦቹ ከወዲሁ ተቀራርበው መወያየትና ከድጎማው ተቋዳሽ መሆን ይገባቸዋል።ፕሪሚየር ሊጉ፣ብሄራዊ ሊጉ እና እታች የሚገኙት ክለቡች ምን ያህል ቀውስ እንደደረሰባቸው በሚገባ ተንትኖ ማቅረብ ይገባል።ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በአፋጣኝ ወደ እንቅስቃሴ ካልተገባ «ሰርገኛ መጣ…»አይነት እንዳይሆን ከወዲሁ ነቅቶ መረጃዎችን መከታተልን ይጠይቃል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 23/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "ce9527f694ae0521632b09fca0b44030" }, { "passage": "ቶክዮ የ2020 ኦሎምፒክ ውድድሮችን ለማከናወን ሁሉን አሰናድታ ዝግጅቷን ማልዳ ብትጨርስም፣ እንደ እንግዳ ደራሽ የሆነው ኮቪድ 19 ኮሮና ቫይረስ በመጨረሻው ሰዓት ድግሷን እንዳይሆን አድርጎታል። ይህም ብቻ አይደለም፣ ለውድድሩ ራሳቸውን በሚገባ እያዘጋጁ የነበሩ፣ ለድልም መንፈሳቸውን ያበረቱ አትሌቶችን ምኞትና ፍላጎት አደብዝዟል። ምንም እንኳ በ2021 ውድድሮች መካሄዳቸው አይቀርም ቢባልም፣ በአስጊነት ማማ ላይ የተቀመጠው ወረርሽኙ በቀጣይ ዓመትስ እንደማይኖር፣ እንደሚጠፋ ምን ዋስትና አለ እየተባለ ነው።ታድያ የወረርሽኙ ስጋት አስቀድሞ ባጠላባቸው አውሮፓ አገራት እግር ኳሱም ተመሳሳይ እጣ ነው የገጠመው። ሁሉም በሚባል ደረጃ ጨዋታዎች የተቋረጡ ሲሆን፣ እስከ ቅርብ ጊዜም ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝመው ነበር። ውድድሮቹ የሚቋረጡ ከሆነ የዓመቱ አሸናፊ ማን ይሆናል? ከታችኛው ከሚባለው ምድብ (ዲቪዚዮን) የሚገኙና ለማደግ ብዙ ወጪ አውጥተው ዓመቱን የተጫወቱ፣ በሊጉ ደግሞ ባላቸው ዝቅተኛ ነጥብ ወደ ታችኛው ምድብ የሚወርዱና መሰል ኹነቶች በቫይረሱ ምክንያት ተዛብተዋል።ታድያ ውድድሮች የሚሰረዙ ከሆነ ዓመቱ እንዳልነበረ ሙሉ ለሙሉ የማጥፋት ያህል የሚቆጠር ነው፣ ለእግር ኳስ ቤተሰብ። ይህ እንዳይሆንም ብዙ ሙግትና ክርክሮች የተካሄዱ ሲሆን፣ የአውሮፓ እግር ኳስ እንቅስቃሴ የጀመረ ይመስላል። የጀርመን ቡንደስ ሊጋም በዚህ ቀዳሚውን እርምጃ ወስዷል። ከኹለት ወር በኋላ በዘመነ ኮሮና የመጀመሪያውን የእግር ኳስ ጨዋታ በዝግ ስታድየም አካሂዷል። ቦርስያ ዶርትሙንድ እና ሻልካ ባደረጉት በዚህ ጨዋታም ዶርትሙንድ አራት ለባዶ አሸንፏል። ደስታው ግን እንደ ወትሮው አይደለም።ይህን በሚመለከት ከቀናት በፊት አልጀዚራ ባስነበበው ዘገባ፣ የጀርመኑ ሊግ ውድድር ይጀምር እንጂ የቀደመ መልኩ ጠፍቷል። ተጫዋቾች ለብቻቸው እንጂ አብረዋቸው ወደ ሜዳ የገቡ ሕጻናት ልጆች የሉም፣ መነካካት አይታሰብም፣ ከዳኞች ጋር መጨባበጥም እንደዛው፣ ጎል አግብቶ መተቃቀፍ ቀርቷል። ጨዋታው ሲደረግ ከክለቦቹ አስፈላጊ ሰዎች፣ እሳት አደጋ ሠራተኞችና ጥቂት ፖሊሶች፣ የስታድየም ጠባቂዎችና ጋዜጠኞች ብቻ ግን ይገኛሉ። በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ማተናገድ በለመደው በግዙፍ ስታድየም ውስጥ ሦስት መቶ ሰዎች ብቻ ተገኝተዋል።በሜዳው ጭንብል ከማድረግ ጀምሮ ተገቢው ጥንቃቄ ሁሉ እንዲደረግ ይጠበቃል። አሠልጣኞች ጮኸው መልእክት ማስተላለፍ ከፈለጉም 1.5 ሜትር ርቀት ላይ ሲሆኑ ብቻ አፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብላቸውን ማውለቅ ይችላሉ። ተቀያሪ ተጫዋቾች ደግሞ ተራርቀው ይቀመጣሉ። ከዛም በላይ አንድም ደጋፊ በስታድየሙ ውስጥ አይገኝም። በጥቅሉ እግር ኳስ ውበቱን በወረርሽኙ ተነጥቋል ማለት ይቻላል። ግን እንዳሉት ከሆነ ምንም ጨዋታ ካለማድረግ እንዲህ ባለ መልኩም ቢሆን መቀጠሉ ይሻላል። በዚህ የማይስማሙ ብዙ ቢሆኑም።አልጀዚራ ታድያ በዘገባው እንዲህ ሲል አስፍሯል፣ ‹‹ደጋፊ በሌለበት ባዶ ስታድየም ጎል ማግባት ይጨንቃል። ተጫዋቾችም ስሜታቸውን እንዲገቱ ነው የሚመከሩት››በኢንግሊዝ ፕሪምየር ሊግም ጨዋታዎች በዝግ ስታድየሞች በቅርቡ ይጀመራሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ቡድኖችም ወደ ልምምድ ገብተዋል። እንደውም ከሰሞኑ በወጣው መረጃ መሠረት የዋትፎርድ እና በርንሌይ ቡድኖች ውስጥ ቫይረሱ ያለባቸው ተጫዋቾች ተገኝተዋል።ቢቢሲ እንዳስነበበው ከሆነ አንድ ረዳት አሠልጣኝን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸው በምርመራ ተረጋግጧል። እነዚህ ሰዎች ራሳቸውን አግልለው ለቀናት እንዲቀመጡ ተመክረው በራቸውን ዘግተዋል። በድምሩም በሊጉ 748 ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ከ19 ክለቦች ምርመራ ተደርጎላቸዋል። እንዲያም ሆኖ ለቤተሰባቸው በመስጋት በቤት ውስጥ ልምምዶችን ማድረግን እንመርጣለን ያሉ ተጫዋቾች ጥቂት አይደሉም።ታድያ ይህ መሆኑ ምንአልባት በቅርቡ የሚለውን የሊጉን መጀመሪያ ጊዜ ሊገፋውና ራቅ ሊያደርገው ይችላል እየተባለ ነው።በኢትዮጵያስ?\nጥቂት የማይባሉ የአፍሪካ አገራት የውድድር ዓመቱን በመሰረዝ ስፖርት ጉዳይ አጀንዳ እንዳይሆን አድርገው ቋጭተውታል። በአፍሪካ ደረጃ የሚደረጉ የሻምፕዮን ውድድሮች የሁሉንም የአፍሪካ አገራት ውሳኔ የሚጠብቁ በመሆናቸው፣ እንደ ስምምነቱ አገራት ውሳኔያቸውን አሰምተዋል።ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊጉን ጨምሮ ሁሉንም ውድድሮች ሙሉ ለሙሉ መዝጋቷ የሚታወስ ነው። ይህም ብዙ ውዝግቦችን እያስነሳ ቢሆንም፣ እስከ ውሳኔው ጊዜ ድረስ ከዚህ የተሻለ አማራጭ አልተገኘም። በዚህም ታድያ ብዙ የእግር ኳስ ቡድኖች የሚከስሩ መሆናቸው ግልጽ ነው። በተለይም ከገንዘብ ጋር በተገናኘ የሚኖሩ ኪሳራዎች ቀላል የሚባሉ አይሆኑም።ከዛም ውጪ ውድድሩ ሙሉ ለሙሉ መቋረጡና የዓመቱ አሸናፊ እገሌ ነው አለመባሉ፣ የአፍሪካ ሻምፕዮና የሚካሄድ ከሆነ በሊጉ የነጥብ ሰንጠረዥ ቀዳሚ ላይ ያለው ቡድን ይሄዳል ወይስ ምን ይደረጋል የሚለውም አንዱ መነጋገሪያ ጉዳይ ነበር። በአንጻሩ የግብጽ ፕሪምየር ሊግ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ ሙሉ ለሙሉ የተሰረዘ ቢሆንም፣ የሊጉ ክለቦች በመስማማት በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ መሪነት ላይ የሚገኝ ቡድን በአፍሪካ መድረክ ይወክለናል በማለት ተስማምተዋል።የአገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ከቡድኖቹ ጋር ተወያይቶ አል አህሊና አል ሞካዉሎ የተባሉ ቡድኖች በአፍሪካ ሻምፕዮና፣ ፒራሚድና ዛማሌክ ደግሞ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ ይሳተፋሉ ብለዋል። ይሁን እንጂ የአፍሪካ ሻምፕዮናም ሆነ የኮንፌዴሬሽን ውድድሮች መካሄድ አለመካሄድቸው ላይ ገና የተባለ ነገር የለም።በኢትዮጵያም የእግር ኳስ ቡድን አመራሮች ተመሳሳይ ውይይት ማድረግ ይገባል የሚል አስተያየትን ሲሰጡ ይሰማል። አንዱ ውሳኔ ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮችን ስለሚያስነሳና ብዙ ውሳኔን የሚፈልግ ጉዳይም ስለሚከተል፣ ሰፋ ያለ ውይይት ማስፈለጉ ጥርጥር የለውም። ይህ በእንዲህ እንዳለ ታድያ የሚታየው መደጋገፍም ቀላል የሚባል አይደለም።በቅርቡ የወጣ ዘገባ እንደሚያስረዳው የቡና እግር ኳስ ክለብ አባላት ያልተከፈላቸውን የአንድ ወር ደሞዝ ቡድኑ እንዲይዘውና የኹለተኛውን ወር ደግሞ ግማሹን ብቻ እንዲከፍላቸው መስማማታቸው ይፋ ሆኗል። ከዛም አልፎ ቫይረሱን ለመከላከል በሚደረግ ጥረት የበኩላቸውን በማድረግም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ተስተውሏል።የፌዴሬሽኖች ፈተና\nየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ከስፖርት ኮሚሽን ጋር በመሆን 70ኛውን የፊፋን ስብሰባ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ነበር። ይህም አሁን ባለንበት ግንቦት ወር ይካሄዳል የተባለ ነው። በእርግጥ ይኸው ዓለም ዐቀፍ የእግር ኳስ ጉባኤ በቪዲዮ ሊካሄድ መወሰኑ ከሰሞኑ ተሰምቷል። ይህንንም ፌዴሬሽኑ በይፋዊ ድረ ገፁ ላይ አስፍሮታል።የእግር ኳስ ብቻ ሳይሆን ታድያ አትሌቴክስ ፌዴሬሽንም ቢሆን ለ2020 የቶክዮ ኦሎምፒክ በዝግጅት ዋዜማ ላይ ነበር። ይሁንና ኦሎምፒኩም ቢሆን ለ2021 ተራዝሟል። በ2021 ራሱ የሚካሄደው ቫይረሱ የጠፋ እንደሆነ እንጂ፣ በዚህ ከቀጠለ ውድድሮ ፈጽሞ ሊሰረዝ ይችላል የሚል ግምት ከወዲሁ እየተሰጠ ነው።\nባሕሩ ጥላሁን፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እንዳሉት ከሆነ፣ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ብዙ ነገር ተቀይሯል። ወረርሽኙም የአመራሩን የዓመቱን እቅድ በሙሉ ነው ያዛባው ብለዋል። የሊግ ውድድሮች በጠቅላላ ታግደዋል። ‹‹ወደ መደበኛ የጊዜ ሰሌዳችን መቼ እንደምንመለስ አናውቅም። በጥቂት ሳምንታት ክረምቱም ይገባል። ሌላ መፍትሄ ካልተገኘ በቀር ሊጉን መጨረስ ከባድ ነው›› ሲሉም አስተያየት ሰጥተዋል።እንደ ፌዴሬሽኑ ከሆነ የዓመቱ አሸናፊ ማን እንደሆነ ሳይታወቅ፣ ከየዲቪዝዮኑ አላፊና ወዳቂው ሳይለይ ሊጉን ማቆም የመጀመሪያ አማራጭ መሆን የለበትም ነበር። ይሁንና ከዛ ውጪ አማራጭ የተገኘ አይመስልም።ክለቦች ታድያ ሁኔታው አልቀለላቸውም። ደሞዝ ለመክፈልም እየታገሉ ይገኛሉ። የክለብ ስፖንሰሮችም ቢሆኑ ከገበያ መቀዛቀዝ ጋር ተያይዞ ስምምነት ለመፈራረም ጊዜውን እያራዘሙ በመሆኑ ክለቦች ገንዘብ ማግኛ ምንጫቸው ሁሉ እየነጠፈ ነው። እንዲያም ሆኖ እንደምንም መክፈላቸውን ቀጥለዋል።በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ፌዴሬሽኑ ካለው ላይ ቀንሶ 500 ሺሕ ብር ቫይረሱን ለመከላከል ለሚደረገው እንቅስቃሴ ድጋፍ አድርጓል። ተጫዋቾችም በቤታቸው ውስጥ ሆነውም እንቅስቃሴ ከማድረግ እንዳይቆጠቡ እያሳሰበም ይገኛል።የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ስጋት ደግሞ ከዚህ ይለያል። ኦሎምፒክን ጨምሮ ሁሉም ዓይነት ውድድሮች በጊዜ ተሰርዘዋል። ከፍተኛ የአትሌቲክስ ሕክምና ባለሞያና የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን የጸረ ዶፒንግ ክፍል ተጠሪ ቅድስት ታደሰ እንደሚሉት፣ ይህ መሆኑ አትሌቶቹን እንዲሁም የአትሌቲክስ አገር የሆነችውን ኢትዮጵያን ይጎዳል። በእነዚህ ውድድሮች አለመሳተፋቸውም አትሌቶችን ብዙ እድል ያሳጣቸዋል። እንቅስቃሴያቸውን እንዲሁም ገቢያቸው ጭምር ይጎዳል።ውድድሮች ሰውነታቸውን እንዲጠብቁ ያግዛቸው ነበር የሚሉት ቅድስት፣ እንደ አገርም በዓለም ዐቀፍ መድረክ ልንታይ የምችልበትን እድል ነው ያጣነው ብለዋል። ከዛ የሚብሰው ደግሞ አትሌቶች ለቫይረሱ የበለጠ የመጠቃት እድል ያላቸው መሆኑ ነው።እንደ ዓለማቀፉ የስፖርት ሳይንስ ባለሞያዎች አስተያየት ከሆነ፣ አትሌቶች በውድድርና በከባድ ሥልጠና ውስጥ ከሆኑ ቫይረሱን የመከላከል አቅማቸው ይዳከማል። ቅድስትም በዚህ ላይ ሐሳባቸውን ሲጨምሩ ከመተንፈሻ አካል ጋር ለሚገናኝ በሽታ ተጋላጭ መሆናቸውን ነው ያነሱት። ‹‹አትሌቶቻችን በሩጫ ጽናታቸው ይታወቃሉ። ይህም የመተንፈስ አቅማቸውን እስከ ጥግ እንዲጠቀሙበት የሚያደርግ ነው። በዚህ ምክንያት ነው ቫይረሱ ምን ያህል ሊያጠቃቸው እንደሚችል መረዳት ያለባቸው›› ብለዋል።የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ታድያ ያለውን የአትሌቶች ትግል እንዲሁም ያለባቸውን ፈተና በመመልከት ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ የሥልጠና ቡድን አባላት፣ 4 ሚሊዮን ብር እና አስፈላጊ የተባሉ የሥልጠና ቅሳቁሶችን አሰራጭቷል። ‹‹ሁሉም 211 ብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድኖችና 56 አሠልጣኖች እያንዳንዳቸው 15 ሺሕ ብር ይከፈላሉ። ይህም ለማበረታቻና ባሉበት ጸንተው ራሳቸውንም እየጠበቁ እንዲቆዩ ነው ለማገዛ ነው።›› ብሏል፣ ፌዴሬሽኑ ባወጣው መግለጫ።ከአዲስ ማለዳ እህት መጽሔት ኢትዮጵያን ቢዝነስ ሪቪው በዐቢይ ወንድይፍራው የተጻፈውን መነሻ በማድረግ ፣ ወቅታዊ ተጨማሪ መረጃዎች ታክለውበት የተዘጋጀቅጽ 2 ቁጥር 81 ግንቦት 15 2012", "passage_id": "a502a9474a8e89c64e46e76599f85f27" }, { "passage": "የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የዓለምን ስፖርት ቁመና ወዳልታሰበ አቅጣጫ የወሰደ ስለመሆኑ እየተነገረ ይገኛል።የስፖርት እንቅስቃሴ ወረርሽኙን መከሰት ተከትሎ መታገዳቸው በስፖርቱ ሊገኙ የሚችሉ በቢሊዮን የሚቆጠር ገቢ ያሳጣው ስለመሆኑ መረጃዎች ያመላክታሉ።ይሄንኑ ዋቢ በማድረግ ወረርሽኙ ስፖርቱን ጥልቅ ወደሆነ የፋይናንስ ቀውስ የዳረገው ስለመሆኑ መናገር ያስችላል።በዘርፍ አዋቂዎች በተደረጉም ጥናቶች«ኮቪድ -19 በስፖርቱ ላይ ያደረሰው ከፍተኛ የሆነ የፋይናንስ ቀውስ መዘዙ ዛሬ ላይ የሚቆም ሳይሆን እስከ ቀጣዮቹ 10 ዓመታት የሚሻገር ይሆናል »የሚሉ መሆናቸውን ልብ ይሏል።የስፖርቱ መስክ በወረርሽኙ ምክንያት ከፍተኛ መቃወስን ያስተናግድ እንጂ ፤ወረርሽኙን ለመዋጋት ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ረገድ ግንባር ቀደሙ እንደነበር ታዝበናል።በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የስፖርት ማህበረሰቡ ወረርሽኙን ለመዋጋት ከነጉዳቱ ትልቅ መስዋዕትነት በማድረግ ለሰብዐዊነት ሰፊ ቦታ የሚሰጥ ማህበራዊ ክዋኔ መሆኑን አስመስክሯል። በሀገራችን በተመሳሳይ የስፖርት ቤተሰቡ በዘመነ ኮሮና ሰብዐዊነትን መሰረት ያደረጉ ተግባራትን በማከናወን ይሄንኑ አስመስክሯል።በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት ፣የስፖርት ማህበራት፣ተጫዋቾች ፣አትሌቶች፣የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል በሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በስፖርት ማህበረሰቡ በኩል ሰብዐዊነትን መሰረት አድርጎ ህዝባዊነትን በመታጠቅ «ወገን ለወገን »ደራሽነቱን በገንዘብና በቁሳቁስ አሳይቷል።በተለይም በክለቦችና በተጫዋቾች በኩል ወረርሽኙን ለመዋጋት ያሳዩትን ቀናኢነት የሚቃረን ተግባር በአንዳንድ ክለቦች እየተፈፀመ ስለመሆኑ መረጃዎች መውጣት ከጀመሩ ውለው አድረዋል። በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ድጋፍ ለሚገባቸው የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች በሚሊዮን ገንዘብ ማበርከታቸውን ሲናገሩ የከረሙ ክለብ ተጫዋቾች «የደመወዝ ያለህ» ሲሉ ቅሬታቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊጉ የሚጫወቱ የተለያዩ ክለብ ተጫዋቾች «ክለቦች ደሞዝ ከለከሉን »ከሚሉት ቅሬታዎች ጀርባ የስፖርት ቤተሰቡ ከገነባው በጎ መልክ ጋር የማይጣጣም እንደሆነ በርካቶች ትችት ሰንዝረዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከደመወዝ ክፍያ ጋር ተያይዞ በክለቦችና በተጫዋቾች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት፣ ክለቦች በገቡት የውል ስምምነት መሠረት የተጫዋቾቻቸውን ወርኃዊ ክፍያ እንዲከፍሉ ያስተላለፈው ተደጋጋሚ መመርያና ማስጠንቀቂያ መፍትሔ ሊሆን እንዳልቻለ የሚናገሩ አሉ፡፡በብሄራዊ ፌዴሬሽኑን መመሪያ መሰረት መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ ማግኘት ካልቻሉ መካከል የሰበታ ከተማ ተጫዋቾች ይገኛሉ።ከሕግና ሥርዓት ውጭ ሆኖ የቆየው የክለቦች የፋይናንስ አሠራር በተለይም ከተጫዋቾች ክፍያ ጋር ተያይዞ እየተነገረ ያለው ጉዳይ ለእግር ኳሱ ተጨማሪ ውድቀት እንዳይሆን የተጫዋቾች ብቻም ሳይሆኑ የክለብ አሠልጣኞች ጭምር ሥጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ ፡፡ከእነዚህ አሰልጣኞች መካከል የችግሩ ባለቤት ከሆኑት መካከል ከሚጠቀሰው የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ከለብን በማሠልጠን ላይ የሚገኘው አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ይገኙበታል ፡፡ አሠልጣኙ የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብን ለማሠልጠን ሲስማሙ ለተጫዋቾች ሊከፈል የሚገባውን ወርኃዊ ክፍያ ጨምሮ በሚያቀርቡት ዕቅድ መሠረት እንዲፈጸም ከክለቡ ጋር ስምምነት እንደነበረው፣ ሆኖም ሥራ ከጀመረበት ዕለት አንስቶ እስካሁን በስምምነቱ መሠረት ሁኔታዎቹ ተፈጻሚ እየሆኑ እንዳልሆነ ያስረዳል፡፡በፕሪሚየር ሊጉ የተለያዩ\nክለቦችን በማሠልጠን የሚታወቀው አሠልጣኝ ውበቱ አባተ የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብን ለማሠልጠን ሲስማማ፣ በዕቅድ ደረጃ የተያዙ በተለይም ክፍያን ጨምሮ የተጫዋቾች አያያዝ፣ ለቅድመ ዝግጅት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችና መሰል ጉዳዮች እንደሚሟሉ ቃል የተገባለት ስለመሆኑ ጭምር ያስረዳል፡፡አሠልጣኙ፣ «ስምምነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በክለቡ ሥራ ሲጀምር ሁለት ዓይነት ማልያና ቁምጣ እንዲሁም ተጫዋቾች በልምምድ ጊዜ የሚለብሱትን መለያ፣ ኮኖዎችን፣ የልምምድ ኳሶችንና ሌሎችም ቁሳቁሶች (ቆይቶ ቢሟሉም) በወቅቱ ግን በግሌ ገዝቼ ነው፡፡ በዚያ ላይ ወደ ክለቡ እንደመጣሁ ያስፈረምኳቸውን ጨምሮ ለሌሎችም ተጫዋቾች የሐምሌ፣ የነሐሴና የመስከረም ወር ክፍያ የተከፈለው ከሦስት ወር በኋላ ነው፡፡ በቅርቡ ወደ ሆነው ስንመጣ ደግሞ የግንቦትና የሰኔ ወር ክፍያ እስካሁን አልተከፈለም፤» ሲል ያስረዳል፡፡በአሁኑ ወቅት ምንም እንኳ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጉዳይ ገና መፍትሔ ባያገኝም፣ ለቅድመ ዝግጅት የሚያስፈልጉ አንዳንድ ጉዳዮች ቀደም ሲል እንደነበረው ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር ለክለቡ አመራሮች ያለፈውን ዓመት ሪፖርት ጨምሮ በቀጣይ ሊሟሉ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ጥያቄ ማቅረቡን ጭምር አሠልጣኙ አልሸሸገም፡፡ምክንያቱን አስመልክቶ አሠልጣኝ ውበቱ፣ «ካለፈው አንድ ዓመት ተሞክሯችን መረዳት የምንችለው በዚህ ሁኔታ ውጤት ከማምጣት ጀምሮ በፕሪሚየር ሊጉ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ለመቀጠል ከባድ ነው፡፡ በዚህ ዓይነት አካሄድና አሠራር አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ክለቡ ለማምጣት ይቸግረኛል፡፡ ምክንያቱም የክለቡ አሠልጣኝ እንደመሆኔ ተጫዋቾች እንዲሟላላቸው የሚጠይቁትን ጥያቄ የማላስፈጽም ከሆነ በእኔ ላይ እምነት ስለሚያጡ፣ በሁለታችን መካከል የሚኖረው ግንኙነት መልካም ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ ማለት በተጫዋቾች ዘንድ ሊኖረኝ የሚገባው ክብር በራሱ ዋጋ እንዳይኖረው የሚያደርግ ነው»ይላል፡፡ ወቅቱ ክለቦች ለ2013 የውድድር ዓመት ዕድሜ ዝግጅት የሚያደርጉበት መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ ክለቦች የሚፈልጓቸውን ተጫዋቾች የሚያዘዋውሩበት ነው:: ከተጫዋቾች ክፍያ ጋር ተያይዞ ችግር የሌለባቸው አንዳንድ ክለቦች ኮንትራት ያጠናቀቁ ተጫዋቾቻቸውን ጨምሮ ሌሎችን ተጫዋቾች እያስፈረሙ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብ አሠልጣኝ ውበቱ እንደሚናገረው ከሆነ፣ ክለቡ የተጫዋቾች ክፍያን ጨምሮ በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ይገኛል:: ሰበታ ከተማ የፊርማን ጨምሮ ወርኃዊ ክፍያን ያጓደለበት ምንም እንደሌለ የሚናገረው አሠልጣኝ ውበቱ አባተ፤«ይህ ለእኔ ምንም ዓይነት እርካታ አይሰጠኝም፣ ምክንያቱም በወርሃዊ ክፍያና በሌሎችም ጥቅማ ጥቅሞች ያኮረፈ ተጫዋች ይዤ የትም መድረስ እንደማልችል ስለምረዳ ነው፤»ሲል የእርሱ ፍላጎት መሟላት የተጫዋቾችን በደል ቸል ብሎ ማለፍ እንደከበደው ያስረዳል ።በሰበታ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች እያሰሙት እንዳለው የደሞዝ ጥያቄ ሁሉ በፕሪሚየር ሊጉ የሚጫወቱ በርካታ ክለቦች ለተጫዋቾቻቸው ደሞዝ ባለመክፈላቸው ተጫዋቾች ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ መዳረጋቸውን መሰማቱ ችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል ።ከእነዚህ መካከል የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ የሚጠቀስ ሲሆን የክለቡ ተጫዋቾች «በኮሮና ቫይረስ ውድድሮች ከተቋረጡ ጀምሮ የሦስት ወር ደሞዛችን አልተከፈለንም »ሲሉ በክለቡ ላይ ቅሬታቸውን ማሰማታቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነበር።ከተጫዋቾች የደመወዝ ቅሬታ ጋር ተያይዞ እየታየ ላለው ሰፊ ችግር የወልዋሎ አዲግራት እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች ተጨማሪ ማሳያ ይሆናሉ።የወልዋሎ አዲግራት እግር ኳስ በተለይ የሀገር ውስጥ ተጫዋቾች ክለቡ «የ4 ወር ደሞዝ ስላልተከፈለን ከነ ቤተሰባችን ለከፍትኛ ችግር ተዳርገናል »ሲሉ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ ነበር ።ክለቡን በፕሪሚየር ሊጉ የተሳትፎ ባለቤት እንዲሆን ማድርጋቸውን አስታውሰው ፤በክፋው ቀን ግን ከጎናቸው ሊሆን አለመቻሉ ትልቅ የሞራል ጉዳት እንዳደረሰባቸው ተናግረዋል።ከወርኃዊ ክፍያ ጋር ተያይዞ ቅሬታ ከቀረበባቸው በርካታ ክለቦች መካከል ጅማ አባ ጅፋር እግር ኳስ ክለብ ሌላኛው ሲሆን፤ክለቡ ለተጫዋቾቹ ደመወዝ ከከፈለ ሰባት ወርና ከዚያም በላይ እንደሆነው በተጫዋቾቹ በኩል ቅሬታዎች ሲቀርቡ እንደነበር ይታወሳል።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሪሚየር ሊጉን ጨምሮ በየደረጃው የሚወዳደሩ ክለቦች በኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ውድድር ቢያቋርጡም፣ ተጨዋቾቻቸውን በተመለከተ ግን በገቡት ውል መሠረት ክፍያ መፈጸም እንዳለባቸው የሚያስገድድ ደንብ አለው፡፡ክለቦች በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት የተቋረጠውን እግር ኳስ እንደገና ለማስጀመር በአንዳንድ ክለቦችና ተጫዋቾች መካከል ከወርኃዊ ክፍያ ጋር በተያያዘ የተፈጠረው ከፍተኛ ችግር እንቅፋት እንደሆነ ይወሳል፡፡ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በክለቦችና በተጫዋቾች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት፣ ክለቦች በገቡት የውል ስምምነት መሠረት የተጫዋቾቻቸውን ወርኃዊ ክፍያ እንዲከፍሉ ያስተላለፈው ተደጋጋሚ መመሪያና ማስጠንቀቂያ መፍትሔ ሊሆን እንዳልቻለ የሚናገሩ አሉ፡፡እንደ ሰበታ እግር ኳስ ክለብም ሆነ ሌሎች ክለቦች ይህንን መመሪያ ተፈጻሚ ለማድረግ ፍላጎት እያሳዩ አለመሆናቸው እየተነገረ ይገኛል ።በተለያዩ ክለቦች በኩል እየቀረቡ ያሉት ቅሬታዎች ጊዜ የማይሰጡ እንደመሆናቸው ብሄራዊ ፌዴሬሽኑም ሆነ ክለቦች በመነጋገር መፍትሄ መስጠት እንደሚኖርባቸው በሙያተኞች በኩል ሀሳብ እየቀረበ ይገኛል።የኮቪድ -19 ወረርሽን ተከትሎ በፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ክለቦች አካባቢ እየታየ ያለው የፋይናንስ መቃወስ ከተጫዋቾች ቅሬታ ተሻግሮ የሀገራችን እግር ኳሱ ህልውና አደጋ ላይ የመውደቁ ተጨባጭ ምልክት ነውና መፍትሄ ማበጀት ይገባል ባይነን።አዲስ ዘመን ሐምሌ10/2012 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "296b20856d18f756824308f17708ecdb" } ]
67b01f858c38d6d0c4efe46d58c9437f
ba98f9daf5ec70deee510e34ba8b92b6
የማይቀረው ውሳኔ ተወስኗል
የመላው ዓለም ሕዝብ ትኩረትና ጭንቀት በሆነው የኮሮና ቫይረስ ፈጣንና አስደንጋጭ ስርጭት የተነሳ መደበኛ እንቅስቃሴዎች በብዙ የዓለማችን አገራት ተገተዋል። የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ለውጦችን ከማስተናገድ አልፎ ሽባ ሆኗል። የስፖርት መገናኛ ብዙኃንም በአንድ ጉዳይ ላይ ብቻ በማጠንጠን ቆመዋል። ቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የሁሉም የስፖርት ቤተሰብ ልብ አንጠልጣይ ጉዳይ ከሆነ ሰንብቷል። ዓለም በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ሆና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩን በተያዘለት ጊዜ ለማካሄድ ድርቅ ማለቱ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል። ያም ሆኖ የዓለም አቀፍ ኮሚቴውን ደረቅ አቋም የሚፈታተን አዲስ ዜና ከየአቅጣጫው ብቅ ማለቱ ትልቅ ተፅዕኖ መፍጠሩ አልቀረም። በተለይም ካናዳና አውስትራሊያን የመሳሰሉ አገራት ከቀናት በፊት ራሳቸውን ከኦሊምፒክ እንዳገለሉ መግለፃቸውን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከግትር አቋሙ እየተለሳለሰ እንዲመጣ አስገድዶታል። ፈረንሳይና እንግሊዝን የመሳሰሉ አገራትም ዓለም አቀፍ ኮሚቴው በአስቸኳይ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ መጠየቃቸውን ተከትሎ ኦሊምፒኩ ላይ ለውጥ ስለመኖሩ በርካቶችን እርግጠኛ ያደረገ ነበር። የኦሊምፒክ ትልቁ ባለድርሻ አካል የዓለም አትሌቲክስ ከቀናት በፊት የቶኪዮ ኦሊምፒክ እንዲራዘም ጥያቄ ማሳቱን ተከትሎም በቅርቡ አዲስ ነገር እንዲጠበቅ አድርጓል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ ኦሊምፒኩ ወደ 2021 የሚሸጋገር ከሆነ በኦሬገን አሜሪካ በተመሳሳይ ወቅት ሊካሄድ ታቅዶ የነበረውን የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ወደ ሌላ ጊዜ ለማስተላለፍ ሙሉ በሙሉ ፈቃደኛ እና ዝግጁ መሆናቸውን ለኮሚቴው ባስገቡት ‹‹ውድድሩ ለሌላ ጊዜ ይተላለፍልን›› መጠየቂያ ደብዳቤያቸው ማረጋገጣቸውም ኦሊምፒኩ እንደሚራዘም ያረጋገጠ ርምጃ ነበር። ይህ ሁሉ ተፅዕኖ የተፈጠረበት የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴም እየመረረውም ቢሆን ውድድሩን ወደ 2021 ለማስተላለፍ ያስገደደውን የማይቀር ውሳኔ ማሳለፉን አሳው ቋል። የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ከትናት በስቲያ ምሽት ባደረጉት የቪዲዮ ኮንፍረንስ ከቫይረሱ ስርጭት ጋር በተያያዘ ያለውን አደጋ ከግምት በማስገባት ኦሊምፒኩ ወደ 2021 እንዲራዘም ውሳኔ ላይ መድረሳቸውን አሳውቀዋል። ኦሊም ፒኩ ወደ 2021 መሸጋገሩ ይጠቀስ እንጂ በየትኛው ወቅት እንደሚካሄድ የተገለፀ ነገር የለም። ያም ሆኖ የበጋ ኦሊምፒክ እንደመሆኑ መጠን በቀጣይ ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ላይ ሊካሄድ እንደሚችል ተገምቷል። ይህንን ውሳኔ ተከትሎም የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ከጦርነት ውጪ ባሉ ምክንያቶች በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተላለፈ ሊሆን ችሏል። ኦሊምፒክ ከጤና ስጋት ጋር የተያያዘ ባይሆንም በተለያዩ ጊዜዎች የመራዘም፣የመሰረዝና የቦታ ለውጥ ሲደረግበት ታይቷል። እኤአ የ1916 የበጋ ኦሊምፒክ በጀርመን በርሊን ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት በአንደኛ የዓለም ጦርነት ሳቢያ ተሰርዟል። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅትም የ1940 የክረምት ኦሊምፒክና የ1944 የበጋ ኦሊምፒክ ውድድሮች የመሰረዝ ዕድል ገጥሟቸዋል። እኤአ የ1976 የክረምት ኦሊምፒክም በዴንቨር ኮሎራዶ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የኮሎራዶ ግዛት ሕዝብ ለውድድሩ የሚወጣውን ወጪ በመቃወሙ ውድድሩ የቦታ ለውጥ ተደርጎበት በአውስትራሊያ ኢንስብረክ ለመካሄድ ተገዷል። ዩ ኤስ ኤ ቱዴይ በወቅቱ እንደዘገበው የኮሎራዶው ኦሊምፒክ የቦታ ለውጥ እንዲደረግበት ውሳኔ ላይ የተደረሰው ውድድሩ ከመካሄዱ ከሦስት ዓመታት አስቀድሞ ነበር። ይህም ከጥንት ጀምሮ የኦሊምፒክ ውድድሮች ላይ የቦታ ለውጥ ለማድረግ ቢያንስ ከሁለት ዓመት በፊት ውሳኔ ላይ መደረስ ይኖርበታል። የሪዮ 2016 ኦሊምፒክም ከመድረሱ ከዓመታት በፊት የዚካ ቫይረስ ስጋት መሆኑ ቢታወቅ ሊሰረዝ፣ሊራዘምና የቦታ ለውጥ ሊደረግበት ይችል እንደነበር በርካቶች አስተያየት ሲሰጡ ይስተዋላል። የዚካ ቫይረስ የሪዮ ኦሊምፒክ ስጋት መሆኑ የታወቀው ውድድሩ ከመካሄዱ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ መታወቁ የቫይረሱ ስርጭት ያን ያህል ስጋት ካለመሆኑ ጋር ተደምሮ የመሰረዝ፣ የመራዘምና የቦታ ለውጥ ሳይደረግበት ለመቅረቱ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን የሚያብራሩም ጥቂት አይደሉም። ዘንድሮም ከአራት ዓመት በኋላ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ከጥር ጀምሮ በቻይና በተቀሰቀሰው የኮሮና ቫይረስ ሳቢያ ተመሳሳይ አደጋ ሊራዘም በቅቷል። አዲስ ዘመን መጋቢት 17/2012
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29163
[ { "passage": "ባሳለፍነው ሳምንት የፕሪምየር ሊጉ ተጫዋቾች የደሞዝ ጣርያን ለመገደብ ከውሳኔ የደረሰው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በተመሳሳይ በከፍተኛ ሊግ እና አንደኛ ሊግ ላይም ውሳኔ ለማሳለፍ የጠራው ስብሰባ ዛሬ ሳይካሄድ ቀርቷል።\nዓለምገና በሚገኘው አንኳር ሆቴል በተጠራው ስብሰባ ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ ጂራ እና ፀኃፊው ኢያሱ መርሐፅድቅ (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን የክለብ ተወካዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በበቂ ሁኔታ ባለመገኘታቸው ምክንያት ወደ ነሐሴ 25 እንዲሸጋገር ከስምምነት ተደርሷል።", "passage_id": "22b25969345a43109b5b3de43f660bba" }, { "passage": "የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያዘዙት የጉዞ ዕገዳ በተመለከተ በበታች ፍርድ ቤቶች ሙግቱ እንደቀጠለ ባለበት በአሁኑ ወቅት ዕገዳው እንደፀና እንዲቆይ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ትናንት ውሳኔ ሰጠ።ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዳኞች ሰባቱ አስተዳደሩን ደግፈው ውሳኔ ሲሰጡ ሁለቱ ዳኛ ሩት ባደር ጊንስበርግ እና ዳኛ ሶኒያ ሶቶማየር ዕገዳው በከፊል እንደታገደ እንዲቆይ ብለዋል።ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔው ላይ የደረሰበትን ምክንያት አልገለፀም።ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለሦስተኛ ጊዜ ያወጡት የጉዞ ዕገዳ አብዛኛው ሕዝባቸው ሙስሊም ከሆኑ ሥምንት ሃገሮች የሆኑ አብዛኞች መንገደኞች እንዳይገቡ ይከለክላል። ሀገሮቹ ቻድ፣ ሊቢያ፣ ኢራን፣ ሶማሊያ፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ የመንና ሰሜን ኮሪያ ናቸው።ይህን የፕሬዚዳንቱን ዕገዳ የሜሪላንድና የሃዋይ ክፍለ ሀገሮች የበታች ፍርድ ቤቶች ዳኞች ሥራ ላይ እንዳይውል አግደውታል።", "passage_id": "f0031f0f3173a5baac1921052077f878" }, { "passage": "ዛሬ ሰኔ 21 ጠዋት 03:00 ላይ በሱሉልታው ያያ ቪሌጅ እንዲካሄድ የተወሰነውን ጨዋታ ለማድረግ ሁለቱም ቡድኖች ፣ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ አባል ፣ የሊግ ኮሚቴ አባታት የተገኙ ሲሆን በድጋሚ ሜዳው ለጨዋታ ለማከናወን አመቺ አይደለም በማለት 05:00 ላይ አዲስ አበባ ስታድየም እንዲካሄድ ተወሰናል ።ከጨዋታው አስቀድሞ በዝናብ ምክንያት ጨዋታው መካሄድ በነበረበት ሰኔ 19 እና 20 ላይ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት ሊመሩ የተመደቡት ፌደራል ዳኛ አለማየሁ ለገሰ እና አራተኛ ዳኛ ፌደራል ዳኛ ኢብራሂም አሊጋዝ እንዲሁም ኮምሽነር ይግዛው ተቀይረው በምትካቸው በዋና ዳኝነት ፌደራል ዳኛ ደረጄ ገብሬ በአራተኛ ዳኝነት ፌደራል ዳኛ ፣ዳንኤል ግርማይ በኮምሽነርት ሸረፋ ዴሌቾ የተመደበ ሲሆን በዚህም የዳኛ እና የኮምሽነር ለውጥ ምክንያት ሱሉልታ ከተማዎች ቅሬታቸውን አቅርበዋል ።05:00 ላይ በአዲስ አበባ ስታድየም የሁለቱም ክለቦች በርካታ ደጋፊዎች በተገኙበት ሞቅ ደመቅ ብሎ የተጀመረው የዕለቱ ጨዋታ በመጀመርያው አጋማሽ ጠንካራ ፉክክር ተስተናግዶበት ጎል ሳይቆጠር ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል ።ከእረፍት መልስ ጨዋታው ተጋግሎ በቀጠለበት ሰአት 57ኛው ደቂቃ ላይ መቀለ የግብ ክልል ውስጥ የሱሉልታው አጥቂ ቶሎሳ ንጉሴ ጥፋት ተሰርቶብኛል በማለት ቢወድቅም የዕለቱ ዳኛ ደረጄ ገብሬ ሆን ብለህ ነው የወደቅከው በማለት የቢጫ ካርድ ሰጥተውት ጨዋታው በቀጠለበት ቅፅበት በዕለቱ ጥሩ ሲንቀሳቀስ የነበረው አማኑኤል ገ/ሚካኤል መቀለ ከተማን ቀዳሚ የምታደርግ ጎል አስቆጥሯል። በዳኛው ውሳኔ ደስተኛ ያልነበሩት ሱሉልታዎች ዳኛውን በመክበብ ተቃውሟቸውን እያሰሙ ባለበት ሰአት አምበሉ ቶሎሳ ንጉሴን ጨዋታውን እንዳልመራ አውከኸኛል በማለት በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ አስወጥተውታል።ከተወሰኑ ደቂቃዎች መቋረጥ በኋላ የቀጠለው ጨዋታ 69ኛው ደቂቃ ላይ አንድ ክስተት ተፈጠረ፡፡ የመቀለው ተጨዋች ሳጥን ውስጥ ያገኘውን ኳስ ወደ ጎል ቢሞክረውም ለጥቂት የግቡን ቋሚ ታኮ ይወጣል፡፡ ሆኖም የዕለቱ ዳኛ ኳሱን ሲመታው ጥፋት ተሰርቶበታል በሚል የፍፁም ቅጣት ምት ሰጥተዋል፡፡ በዳኛው ውሳኔ የተበሳጩት ሱሉልታዎችም ጨዋታውን አንጫወትም በማለት ሜዳውን ለቀው ወጥተዋል። የዕለቱ ዳኛ ከኮሚሽነሩ እና የሁለቱም ቡድኖች አምበሎች ጋር ተነጋግረው ጨዋታው 69ኛው ደቂቃ ላይ ሊቋረጥ ችሏል።ኮሚሽነሩ ከሚያቀርቡት ሪፖርት ተነስቶ የሊግ ኮሚቴው በተቋረጠው ጨዋታ ዙርያ ምን እንደሚወስን ወደፊት የሚገፅ ይሆናል ።በዚሁ ዕለት አስቀድሞ እንዲካሄድ የተወሰነው የመቀለ ከተማ እና የባህርዳር ከተማ ጨዋታ በሱሉልታ እና መቀለ ጨዋታ ምክንያት ወደ ሌላ ጊዜ ሲሸጋገር ባህርዳር ከተማዎች የቀን ለውጡ የተነገረን በደብዳቤ ሳይሆን በስልክ በመሆኑ ብንቀር ፎርፌ ይሰጥብናል በማለት ባህርዳር ከተማዎች ተገኝተው የነበረ ቢሆንም ጨዋታው ሰኔ 27 እንደሚካሄድ ተነግሯቸው ተመልሰው ሄደዋል።አሁን ላይ በተገኘው መረጃ መሰረት የዛሬው ጨዋታን የመራው ደረጄ ገብሬ ላይ ቅጣት መጣሉ የተነገረ ሲሆን የውሳኔዎቹን ዝርዝር እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል፡፡", "passage_id": "73dff0aba040b1eb1c3e453c8b48959c" }, { "passage": "የኢትዮዽያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ብዙ የተጠበቀው ጠቅላላ ጉባዔን ካካሄደ በኋላ ምርጫው ለ45 ቀናት እንዲራዘም መወሰኑ ትኩሳቱን ለተጨማሪ ጊዜያት ያባባሰው መስሏል፡፡ ጉባዔው ተጠናቆ ብዙም ሳይቆይም ከወዲሁ ለውጦች እየታዩ ነው፡፡ከጠቅላላ ጉባዔው ዋዜማ አንስቶ አስገራሚ የሆኑ መረጃዎች ሲወጡ ቆይተዋል፡፡ ከፊፋ ጋር በግል የተደረጉ የደብዳቤ ልውውጦች ፣ የማህተም እገዳ ፣ በስራ አስፈፃሚዎች እና በፕሬዝዳንቱ መካከል ከቡጢ መሰናዘር እስከ የውሀ ኮዳ መወራወር የደረሰ ክፍፍል እስከ ጠቅላላ ጉባዔው መዳረሻ ዘልቋል። በሁለት ቀን ውሎው ምንም እንኳ የኮዳዎች መወራወር ባይኖርም የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተክለወይኒ ጉባዔው ሊደረግበት ስለታሰበው ቦታ ያደረጉት አወዛጋቢ ንግግር የስፖርት ቤተሰቡን ያሳዘነ ተግባር ሆኖ አልፏል። ጉባዔው ሰመራ እነንዲካሄድ የታሰበው የሚድያ “ጭፍጨፋ”ን ለመሸሽ እንደሆነ ፣ በመጀመርያ አስበው የነበረው መቀለ ከተማ ላይ እንዲካሄድ መሆኑን መናገራቸው እና የጉባዔው መቀለ መካሄድን አስፈላጊነት ከከተማው ቆነጃጅት ጋር ማያያዛቸው ውግዘት አስከትሎባቸዋል፡፡ታዲያ ከጉባዔው መጠናቀቅ በኋላ ምሽቱን የትግራይ እግርኳስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ እጩ የነበሩት አቶ ተክለወይኒ አሰፋን ማንሳቱን ይፋ አድርጓል፡፡ ያቀረበው ምክንያትም ያደረጉት ንግግር ክልሉን የማይወክል ነው የሚል ነው፡፡የአቶ ተክለወይኒን ከእጩነት መነሳት ተከትሎ ሌሎች ክልሎች የዕጩ ተወካዮቻቸውን ሁኔታ ለማጤን እያሰቡ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ በተለይ ዛሬ በድሬዳዋ መገናኛ ብዙሀን ሲገለፅ እንደተሰማው ከሆነ በከተማ አስተዳድሩ እጩ ሆነው የቀረበት አቶ አበበ ገላጋይ በከተማው ነዋሪ ከፍተኛ ትችት እየቀረበባቸው እንደሆነ እና እጩ ሆነው የተላኩበት መንገድም አሳማኝ እንዳልሆነ ተነግሯል፡፡ ይህን ተከትሎም በዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ የድሬዳዋ ከተማ አመራሮች በአቶ አበበ ጉዳይ ላይ ሊወስኑ እንደሚችል እየተጠበቀ ነው።ድሬዳዋ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ክልሎችም የትግራይ ክልል እግርኳስ ፌዴሬሽን ውሳኔ ያነቃቸው ይመስላሉ፡፡ በቀጣይም አስቀድመው እጩ ሆነው በቀረቡ ተወካዮች የተመረጡበትን መንገድ ሊያጤኑበት እንደሆነም ሰምተናል።የአቶ ተክለወይኒ አሰፋን ከእጩ ተወካይነታቸው ያነሳው የክልሉ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ መሆኑ የመንግስት ጣልቃ ገብነት አለው በሚል ወደ ህግ ሊያመሩ እንደሚችል እየተሰማ ይገኛል ።", "passage_id": "36b4d1d47e8d03ab8e7e7135307fc484" }, { "passage": " የ27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር የነበረው የኢትዮጵያ ቡና እና መቐለ 70 እንደርታ ጨዋታ ሳይካሄድ ከቀረ በኋላ መቼ ፣ የት እና በምን ሁኔታ ይደረግ የሚለው ጉዳይ ዕልባት ሳያገኝ መቅረቱ ይታወቃል። ፌዴሬሽኑ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ በጁፒተር ሆቴል በሰጠው መግለጫ ጨዋታው ትናንት በአዲስ አበባ ስታድየም በዝግ እንዲካሄድ ወስኖ ነበር፡፡ ሆኖም ኢትዮጵያ ቡና በዝግ ስታድየም የሚጫወትበት ምንም አይነት የህግ አግባብ እንደሌለ በመግለፅ ጉዳዩን እስከ ፊፋና የስፖርት ግልግል ፍርድ ቤት እንደሚያደርሰው አሳውቆ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው የፌዴሬሽኑ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ትናንት ሌላ ተጨማሪ ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት ተገዷል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ቡና ከመቐለ 70 እንደርታ የሚያደርጉት ጨዋታ ወደ ማክሰኞ ተዘዋውሮ አዲስ አበባ ላይ በክፍት ስታድየም እንዲካሄድ ወስኗል፡፡ በፀጥታ ስጋት ምክንያት በተደጋጋሚ ሳይካሄድ የቆየው ይህ ጨዋታ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ በሚገኘው ፈተና ምክንያት በፀጥታ አካላት ላይ ጫና በመኖሩ ፈተናው ከተጠናቀቀ በኋላ ጨዋታው እንዲካሄድ ፖሊስ በመጠየቁ ለማክሰኞ መዘዋወሩን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ አስታውቀዋል። ፖሊስም ሆነ የእግር ኳስ ክለቦቹ ኃላፊነት የሚወስዱ መሆናቸውን በመግለፃቸው ጨዋታው ደጋፊዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ስታድየም እንደሚካሄድም አክለዋል ።‹‹ጨዋታው\nእንዲቋረጥ የተደረገው በጸጥታ\nአካላት መሆኑ ይታወቃል፣\nከዛም የወሰነው ውሳኔ\nደንብ እና መመሪያውን\nየተከተለ ነው፤ በእርግጥ\nበአሰራር ላይ የተፈጠረ\nክፍተት አለ፤እያንዳንዳችን የየራሳችን\nክብር አለን ሚዲያ\nየቤቴ ጓዳ ጎድጓዳን\nግን ገብቶ ሊያወራ\nአይችልም ፤ በመጀመሪያው\nዙር መቐለ ላይ የተፈጠረውን አላየሁም ብሎ ሪፖርት\nያደረገው ኮሚሽነር ላይ እርምጃ\nባለመውሰዳችን ይቅርታ እጠይቃለሁ››\nበማለት የተናገሩት አቶ ኢሳያስ፣\nየኢትዮጵያ ቡና በመቐለ\nስታዲየም የደረሰበት ኢ-ስፖርታዊ\nድርጊት በጊዜ ውሳኔ\nባለማግኘቱ ይቅርታ ከመጠየቅ\nባሻገር በጥቂት ቀናት\nውስጥ በመቐለ 70 እንድርታ\nላይ እርምጃ እንደሚወስድ\nአብራርተዋል፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 8/2011", "passage_id": "be66af359400254cd5edd5c42b0a5c52" } ]
af74d61e304e94439a7791f53e23d53f
181f65790ddfc27c25d67d6cdd582fd3
ለእጅ ኳስ ስፖርት 40 ዓመታት የተዘረጉ እጆች
በኢትዮጵያ የእጅ ኳስ ስፖርት ታሪክ ውስጥ አንቱታን ማትረፍ ችለዋል። የእጅ ኳስ ስፖርትና እርሳቸው የሚነጣጠሉ አለመሆኑን ብዙዎች ይመሰክሩላቸው። ለእጅ ኳስ ስፖርት ጥልቅ ፍቅር ያላቸው ኢንስትራክተር አሰፋ ገለቱ። በእጅ ኳስ ስፖርት በብሄራዊ ቡድን ደረጃ ተጫውተው ከማለፍ ባሻገር በርካታ ወጣት አሰልጣኞችን ማፍራት መቻላቸው ለዚህ ክብር እንዲበቁ አድርጓል። የኢንስትራክተር አሰፋ የስፖርት ህይወት ጅማሮ ከ40 ዓመታት በፊት እንደነበር እንዲህ ይናገራሉ። «ስፖርታዊ እንቅስቃሴን የጀመርኩት በሰፈር ውስጥ ሲሆን ከልጅነት ጀምሮ ንቁ ተሳትፎ አደርግ ነበር። በስፖርቱ የነበረው ተሳትፎ ግን እግር ኳስን ያስቀደመ ነው።›› ኢንስትራክተር አሰፋ ከእግር ኳሱ እኩል ቅርጫት ኳስ እና እጅ ኳስን ይጫወቱም ነበር። በተለያዩ ስፖርቶች ተወጥሮ የነበረው የስፖርት ፍቅር በአንድ አጋጣሚ ነበር ወደ እጅ ኳሱ ብቻ ሊያመዝን እንደቻለ የሚናገሩት፡፡ ‹‹በወቅቱ ከአዲስ አባባ ፖሊስ የእጅ ኳስ ቡድን ጋር በመሆን እጅ ኳስ እጫወት ነበር። ከቡድኑ ጋር አደርገው በነበረው እንቅስቃሴ ከቡድኑ ተጫዋቾች ብሎም አሰልጣኞች በእጅ ኳሱ እንድገፋበት አድርጎኛል። በዚህ ግፊት የአዲስ አበባ ፖሊስ የእጅ ኳስ ቡድንን በመቀላቀል ወደ እጅ ኳስ ስፖርት ሙሉ ለሙሉ መግባት ቻልኩ›› ይላሉ። ኢንስትራክተር አሰፋና እጅ ኳስ በዚህ መልኩ ትውውቅ ካደረጉ በኋላ በበርካታ የከተማ አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ውድድሮች ላይ የመጫወት እድሎችን አገኙ። በእጅ ኳሱ የተጫዋችነት ሂደት ውስጥ ከክለብ ባለፈ እስከ ብሔራዊ ቡድን ውክልና ዘልቋል፡፡ ለኢትዮጵያ የእጅ ኳስ ብሄራዊ ቡድን በመመረጥ ለአምስት ዓመታት እስከ መጫወትም ደርሰዋል፡፡ ኢንስትራክተር አሰፋ በተጫዋችነት ብቻ 20 ዓመታት ማሳለፍ የቻሉ ሲሆን በእነዚህ ዓመታት ውስጥ «በተጫዋችነት ዘመኔ የማይቆጩኝን 20 ዓመታትን አሳልፌያለሁ። በስፖርቱ ሀገሬን በመወከል በብሄራዊ ቡድን ደረጃ የተጫወትኩበት እነኚህ ዓመታት ለእኔ ልዩ ኩራቴና ትዝታዎቼ ነበሩ» ሲሉ ያለፈውን የተጫዋችነት ዘመን ያስታውሳሉ፡፡ ለሀገር ክብርና ፍቅር እንዳላቸው ደጋግመው የሚናገሩት ኢንስትራከተር አሰፋ የተጫዋችነት ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ አሰልጣኝነት ነበር የተሸጋገሩት። ኢንስትራከተር አሰፋ በእጅ ኳሱ አሰልጣኝ በመሆን በአዲስ መንፈስ እንዴት ብቅ እንዳሉ ሲያስታውሱ፤ «የእጅ ኳስ አሰልጣኝነትን የአዲስ አበባ ፖሊስ እጅ ኳስ ቡድን በመያዝ ነበረ የተጀመረው። ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በርካታ ጊዜያትን ካሳለፍኩኝ በኋላ ቀጣዩ መዳረሻዬ የነበረው ኦሜድላ ነበር» ይላሉ። የኦሜድላን እጅ ኳስ ቡድን ወደ ማሰልጠኑ መሸጋገራቸው ለስፖርቱ የሚያበረክቱትን አስተዋፅኦ እንዲጨምር እንዳደረገላቸው ይናገራሉ። በኢትዮጵያ የእጅ ኳስ ታሪክ በተለይ በ70ዎቹ ውስጥ በጥንካሬያቸው ከሚጠቀሱት ክለቦች መካከል ኦሜድላ ዋነኛው ነው። ከክለቡ ጋር በነበራቸው ቆይታ ስፖርቱን ወደ ፊት ማራመድ የሚያስችሉ ስራዎችን ለመስራት እንዳስቻላቸው ኢንስትራክተር አሰፋ ይናገራሉ፡፡ በአሰልጣኝነት ቆይታቸው ጊዜ እየተመዘገቡ ባሉ ውጤቶች ደስተኛ የነበሩት ኢንስትራክተር አሰፋ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የእጅ ኳስ ስፖርት መዳከምና ውጤት አልባ እየሆነ መምጣት በቁጭት እንዲሞሉ ያደረጋቸው ነበር። በወቅቱ ስፖርቱ ረጅም ዓመት እንደቆየ ባለሙያ መፍትሄ መፈለግ እንደሚገባ ለሚመለከተው አካል ሃሳብ እስከ ማቀበል መድረሳቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በሃሳብ ብቻ መወሰን ግን አልፈለጉም ነበር ። ከኦሜድላ ክለብ ጋር የነበራቸውን ጉዞ በመግታት መፍትሄው ላይ ወደ ማነጣጠር አዘነበሉ፡፡ ስፖርቱን መሰረት አሳጥቶ ውጤት አልባ ያደረገው የተተኪ ችግር እንደሆነ በማጥናት ታዳጊዎች ላይ መስራት ይጀምራሉ፡፡ በ1990 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ውጤት ያጣውን የእጅ ኳስ ስፖርት ለመታደግ ታዳጊዎችን መሰረት ያደረገውን ተግባር በቁጭት ጀመሩ። ከአዲስ አበባ እጅ ኳስ ፌዴሬሽንና ከሙያ አጋሮቻቸው ጋር በመቀናጀት ታዳጊዎችን በፕሮጀክት ደረጃ በማቀፍ ስልጠናዎችን በስፋት መስጠት ተያያዙት፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥም ውጤታማ ስራዎች ማከናወን ቻሉ፡፡ የኢንስትራክተር አሰፋ ታዳጊዎችን መሰረት ያደረገ ስልጠና በትምህርት ቤቶች ላይ ትኩረት አድርጎ ወደ መስራት ሽግግር ያደረገ ነበር። በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የሚገኙ የአንድኛና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን በመመልመል የእጅ ኳስ ስፖርት ወደ ማሰልጠን ነበር የተሸጋገሩት። ኢንስትራክተር አሰፋ ትምህርት ቤቶች ላይ መሰረት በማድረግ በርካታ ታዳጊዎችን አሰልጥነው ማስመረቅ እንደቻሉ ይናገራሉ። «የአምናውን ብቻ ብናስታውስ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ የሆኑ 300 ታዳጊዎችን በፕሮጀክት ደረጃ በማሰልጠን ተመርቀዋል።በዘንድሮ ዓመትም በተመሳሳይ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ከ20 በላይ መንታዎች ሰልጠነው ተመርቀዋል» ሲሉ ይናገራሉ። በእጅ ኳስ ስፖርት ውስጥ ትልቅ አሻራ ማሳረፍ የቻሉት ኢንስትራክተር አሰፋ፤ የስፖርት ህይወት ጉዞን አስደናቂ የሚያደርገው ለስፖርቱ እድገት ታዳጊዎችን መሰረት አድርጎ መስራት እንደሚበጅ በማመን በሰሩት ውጤታማ ተግባር የተቸራቸው ምስጋና ሳያባራ፤ በሀገራችን ባልተለመደ መልኩ መስማት የተሳናቸውን ዜጎች እጅ ኳስ ለማሰልጠን የሚያስችል ንድፈ ሀሳብ በመያዝ መስማት የተሳናቸውን ታዳጊዎች ማሰልጠን መጀመራቸው ነው፡፡ ኢንስትራክተር አሰፋ ለዚህ እንደመነሻ የነበራቸውን አጋጣሚ ሲያስረዱ፤« በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ስልጠና በሚሰጡበት ወቅት የታዘብኳቸው ነገሮች ወደዚህ እንድገባ ያደረጉኝ። ለተማሪዎች እጅ ኳስ ስልጠና በምሰጥበት ወቅት እዛ አካባቢ መስማት የተሳናቸው እኔ የምሰጠውን ስልጠና ቁጭ ብለው ይመለከቱ ነበር። በእነዚህ ታዳጊዎች ተግባር ውስጤ ተነሳሳ። ስልጠናውን ወደ መስጠት ከመሸጋገሬ በፊት ግን ከተማሪዎቹ ጋር ለመግባባት እንድችል የምልክት ቋንቋ መቻል አስፈላጊ ነበር። በመሆኑም ቋንቋውን ለሶስት ወራት ያህል ተማርኩ። በዚህ መሰረት በአዲስ አበባ መስማት የተሳናቸውን ተማሪዎች ከሚያስተምሩ ሶስት ትምህርት ቤቶች ጋር በመነጋገር እንዲሰለጥኑ ማድረግ ችያለሁ» ይላሉ፡፡ ኢንስትራክተር አሰፋ በእጅ ኳስ ስፖርት ውስጥ ያከናወኗቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት ቢሆኑም እሳቸው ዛሬም በአዲስ ወኔ ለመስራት ያሰቧቸው ስራዎች መኖራቸውን ይናገራሉ። «ስፖርት ለእኔ ህይወቴ ነው፤ ልጅነቴን ፣ ወጣትነቴን ከእጅ ኳስ ስፖርት ሳልነጠል አሳልፌያለሁ። ዛሬም ነጭ ፀጉር አብቅዬም ከስፖርቱ መለየት አልሻም። ስፖርቱን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ አማራጭ ያልኳቸውን ተግባራት ለማከናወን አልተኛም» የሚል ጽኑ እምነት አላቸው። ስፖርቱን ለማሳደግ እንደ እርሳቸው ሁሉ በርካታ ባለሙያዎች ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸውና ለዚህ ደግሞ ስፖርቱን ከሚመሩት አካላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ የሚገባ መሆኑን ማስገንዘብ እንደሚፈልጉ ያብራራሉ፡፡አዲስ ዘመን መጋቢት 15/ 2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29023
[ { "passage": "በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ አይረሴ ተጫዋቾችን በማፍራት የሚታወቀው መሳለሚያ አካባቢ የሚገኘው <ኳስሜዳ> ከ25 ዓመታት በፊት በልማት ምክንያት ወደ ትምህርት ቤት መቀየሩ ይታወሳል። ከዛ ወዲህም ኳስሜዳ ለአካባቢው ስያሜ ብቻ ሆኖ ቀርቷል።በ2001 ከትምህርት ቤቱ ጀርባ ምትክ ቦታ ተሰጥቶ ሜዳውን ለመስራት የመሰረት ድንጋይ ተጥሎ የነበረ ቢሆንም ቦታው እንደታሰበው የእግርኳስ ሜዳ እንዳይሆን እና ሌላ የልማት ስራዎች እንዲሰራበት ለማድረግ ጥረቶች ተደርገዋል። ሆኖም የአካባቢው ነዋሪዎች ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት በቅርቡ በአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ መልካም ፍቃድ ቦታው ላይ የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራ እንዲሰራበት ፍቃድ ማግኘቱን፣ የካርታ ርክክብ በቅርቡ እንደሚፈፀም እና የፉትሳል ሜዳውን ለመጀመር ማሰባቸውን የኳስሜዳ ኮሚቴ አስተባባሪ ለኢትዮ ኤሌክትሪክ (ከ1983 – 86) መጫወት የቻለውና በአሁኑ ወቅት አቢሲኒያ የተባለ የታዳጊዎች ፕሮጀክት በመክፈት እየሰራ የሚገኘው ሞገስ ታደሰ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግሯል።በቅድሚያ ኳስሜዳ በኢትዮጵያ እግርኳስ ያበረከተውን ውለታ እንዴት ትገልፀዋለህ?  የዛሬን አያርገውና ኳስሜዳ በኢትዮጵያ እግርኳስ ስማቸው የማይረሳ ብርቅዬ ተጫዋቾችን ያፈራ ሜዳ ነው። ኃይሌ ካሴ፣ ወርቁ ማሞ፣ ሀሚቲ ካሳ፣ አስቻለው ተሰማ እና አቦነህ ማሞ ያደጉበት ከቅርቦቹ እነ ዓሊ ረዲ፣ ማሞዓለም ሻንቆ እና ሌሎችም ዝነኛ ተጫዋቾች የወጡበት ሜዳ ነበር።  ሆኖም የዛሬ 25 ዓመት “ለአቅም ግንባታ” በሚል የተወሰነው የሜዳ ክፍል ግንባታ ተከናወነበት። በቀረው የሜዳ ክፍል የአካባቢው ወጣቶች እና ታዳጊዎች እየተጫወቱበት ቆይቶ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በአካባቢው ብዙ ትምህርት ቤቶች እያሉ ሜዳው ላይ ትምህርት ቤት በመስራታቸው ይህ ታሪካዊ ሜዳ በሚያሳዝን ሁኔታ ጠፍቷል። በወቅቱ አስታውሳለው ብዙ ህዝብ በዚህ ነገር በመበሳጨት ትምህርት ቤቱ እንዳይሰራ እና ሜዳው እንዲቆይ ጥረት አድርገናል። ቆፍረው ሲሄዱ መልሰን አፈር እያለበስን ሜዳውን ለማስቀረት ብንሞክርም ትታሰራላቹ የሚል ማስፈራርያ ይደርስብን ነበር።  ሆኖም ይህ ጥረታችን ሳይሳካ በመቅረቱ ነዋሪው በጣም አልቅሶ፣ አዝነን ሜዳውን ተነጥቀናል። አሁን ላይ ኳስ ሜዳ ደብዛው ጠፍቶ ስናይ ሁሌም ያሸማቅቀናል።ይህ ታሪካዊ ሜዳ በልማት ምክንያት በመቅረቱ በትውልዱ ላይ ያሳደረው አሉታዊ ጎን አለ ትላለህ?ይህ ሜዳ በልማት ምክንያት ከቆመ በኋላ  አንዳንድ ወጣቶች በሚያሳዝን ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ። በተለያዩ ሱሶች እየተጠቁ ይገኛል። ከመጠን በላይ አላስፈላጊ ባህሪ ውስጥ የገቡ ወጣቶች አሉ። የሚያሳዝነው የአዕምሮ ህመምተኛ የሆኑም ጭምር መኖራቸው ነው። ታዲያ ይሄንን ሁሉ እያዩ መኖር ልብን ይሰብራል። ትውልድ ጠፍቷል፤ ለኢትዮጵያ እግርኳስም ሀዘን ነው ማለት ይቻላል።\nአሁን ዘመናዊ የፉትሳል ሜዳ ለመስራት አቅዳችኋል። ታዲያ ይህን መሬት እንዴት ልታገኙ ቻላችሁ?ይህ ቦታ የከብቶች ማደለብያ ቦታ ነበር። በተለያዩ መንገዶች ቤቱ ስራ አቁሞ ሲዘጋ እዚህ ቦታ ላይ ቢያንስ አስር ሰው የሚጫወቱበት የፉትሳል ሜዳ እንዲሰራ ለክፍለ ከተማው ጥያቄ አቀረብን። በወቅቱ የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበሩት ኩማ ደመቅሳ ይህን ቦታ እንድንሰራበት ፈቅደው የመሰረት ድንጋይ 2001 ሰኔ 7 ላይ ተቀምጦበታል።ታዲያ ላለፉት አስር ዓመታት ቦታው ላይ የታሰበው የፉትሳል ሜዳ ሳይሰራ ለምን ቀረ?ብዙ ውስብስብ ነገሮች አሉበት። በወቅቱ የነበረውም ብልሹ አሰራር ይመስለኛል ግንባታው እንዳይካሄድ ያደረገው። በተለይ አንዳንድ ባለ-ሀብቶች ቦታው ግንባር ቦታ በመሆኑ ለልማት ለመውሰድ ብዙ ጥረት አድርገው ነበር። በከተማ አስተዳደር ያሉትም አመራሮች ቦታውን ለባለ-ሀብት ለማስተላለፍ ሞክረዋል። ሆኖም የአካባቢው ነዋሪ ይህ ቦታ እንዳይወሰድ ባደረገው ከፍተኛ ጥረት እና ጫና ከብዙ ትግል በኋላ ተሳክቶ ቦታውን አስከብረን እንዳይወሰድ ማድረግ ችለናል። አመራሮቹም የነበረንን ቆራጥነት ተመልክተው ምንም ነገር ሳያደርጉት ቦታው ላይም ምንም ነገር ሳይሰራበት አስጠብቀን ለአስር ዓመት አቆይተናል።ከሰሞኑን ቦታውን በተመለከተ አንድ ተስፋ ሰጪ ነገር እንዳገኛችሁ ሰምተናል። ይህ ነገር ምንድነው?በመጀመርያ የኳስ ሜዳ ህዝብ ብዙም ፖለቲካ ውስጥ አይገባም፤ አይሳተፍም ይሄም ይመስለኛል ያለፉትን ዓመታት ቦታው እንዲወሰድ እና ኳስ መጫወቻ እንዳይሰራበት የተፈለገው። ለመጀመርያ ጊዜ ነው የአካባቢው ነዋሪ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ የሆኑት ታከለ ኡማን ያመሰገነው። እውነት ለመናገር በአጭር ጊዜ ውስጥ ያቀረብነውን ጥያቄ ተቀብለው፣ አስፈላጊውን ድጋፍ ለመፈፀም ቃል በመግባት ቦታው ላይ ዘመናዊ የፉትሳል ሜዳ እንድንሰራ በአስቸኳይ የማረጋገጫ ካርታ እንዲሰጠን የተባበሩን በጣም እናመሰግናለን። ይህ ለእኛ እና ለታዳጊው ትልቅ ተስፋ ነው።\nከከተማው መስተዳድር የቦታውን ማረጋገጫ ካርታ በቅርቡ ትረከባላችሁ። ስለዚህ ወደ ግንባታው መቼ ትገባላችሁ?  በምን ያህል ጊዜ ለማጠናቀቅ አስባችኋል? ለግንባታው የሚሆን የፋይናንስ ምንጭ እንዴት ለማግኘት አስባችኋል?  በዚህ ስራ ክፍለ ከተማውም ሆነ ወረዳው ለግንባታው ድጋፍ ለማድረግ በጀት እንደሚመድቡ ቃል ገብተውልናል። ይህ ጥሩ ነገር ቢሆንም እንደሚታወቀው ከመንግስት የሚለቀቁ ገንዘቦች በፍጥነት ስለማይለቀቁ እና የሚቆራርጡ በመሆናቸው አስቸጋሪ ነው። ይህ ቦታ የሜዳ ግንባታ እንዲካሄድበት የለፉ የደከሙ በሀገር ውስጥም በውጭም አሉ ይህንን ቦታ ሜዳ ለማድረግ ሁሉም ጓጉቷል። የአካባቢው ነዋሪም ከፍተኛ ፍላጎት ያለው በመሆኑ በተቀናጀ ሁኔታ ለመስራት ከማኅበረሰቡ የተወጣጡ ስምንት አባላት ያሉበት ኮሚቴ ተዋቅሯል። ከወረዳው ስፖርት ፅህፈት ቤት ጋር በጋራ በመሆን ሰፊ ውይይት አድርገን ካርታው እጃችን እንደገባ ወደ ስራ የምንገባ የሚሆነው። ሁሉም ሰው ተሰርቶ እንዲያልቅ ካለው ጉጉት የተነሳ ይረባረባል ብዬ ተስፋ አደርጋለው። በቀጣይም ዝርዝር ነገሮች እናቀርባለን።በመጨረሻም የምታስተላልፈው መልክት ካለ?የኳስ ሜዳ መጥፋት የብዙ ሰው ቁጭት፣ ሀዘን ነው። ሁሉም ሰው ይህ የፉት-ሳል ሜዳ ተሰርቶ ማየትን ይፈልጋሉ። ኳስ ሜዳ የድሮ ስሙን ይዞ ጤናማ አዕምሮና ሙሉ አካል ያላቸው ወጣቶች የሚፈሩበት ቦታ እንደሚሆን እተማመናለው።", "passage_id": "d93fef0998ae8c9d8a4b58ae859883e2" }, { "passage": "ወርቃማ በሚባለው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ዘመን የያኔው ሐረርጌ ክፍለ ሃገር ክለቦች የብሔራዊ ቡድኑ ጥንካሬና የጀርባ አጥንት በመሆን ዛሬ ላይ የምንዘክራቸው በርካታ ከዋክብት ተጫዋቾችን አበርክተዋል። በ1952፣ 54፣ 55 እና 57 ዓ.ም ለአራት ዓመት ጥጥ ማህበር (ኮተን)፣ ከ1953 እስከ 1956 ደግሞ ድሬዳዋ ሲሚንቶ ከክልላቸው አልፈው የኢትዮጵያ ቻምፒዮን ሆነዋል። በ1990 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በቂ ጥናት ሳይደረግበት፣ ያለ ጊዜው ከተወለደ በኋላ የከተማ ወይም ክልል ቻምፒዮናዎች ቀስ በቀስ ደብዛቸው እየጠፋ ሄዷል። የከረረው የድሬ ጸሐይ ሳይበግረው በየሳምንቱ የከተማውን ክለቦች ፍልሚያ ይመለከት የነበረው የዚያ ዘመን ትውልድ እግር ኳስ አፍቃሪ ዛሬ በአንድ ክለብ ብቻ ቀርቶ በሁለት ሳምንት አንድ ጊዜ የድሬዳዋ ከተማ ጨዋታን ብቻ መመልከት እጣፋንታው ሆኗል። ይህም አንድ ለእናቱ የሆነው የድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ለበርካታ ዓመታት ፕሪሚየር ሊግ ላይ ተሳታፊ መሆን ተስኖት ምስጋና ለሴቷ አሰልጣኝ መሰረት ማኔ ይሁንና ከሦስት ወይም አራት ዓመታት ወዲህ ነው በፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ለመሆን የበቃው። አሁንም ቢሆን ድሬዳዋ ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ ከዓመት ዓመት ላለመውረድ እንጂ ለዋንጫ ተፎካካሪ ክለብ ሆኖ ደጋፊዎቹን የሚያረካና የሚመጥን ደረጃ ላይ መድረስ አልቻለም። እንደ ድሬዳዋ ሁሉ\nየአዲስ አበባ\nእግር ኳስም\nፕሪምየር ሊግ\nአመጣሽ በሆነ\nነቀርሳ ቀስበቀስ\nወደ ሞት\nእያዘገመ ነው።\nበሊጉ ላይ\nየአዲስ አበባ\nክለቦች ቁጥር\nእያደር እየከሰመ፣\nተጽኗቸውም እየተዳከመ\nሄዷል። የዚያኑ\nያህል በከተማዋ\nየነበሩ ትልልቅ\nክለቦች ከዓመት\nዓመት ከአይን\nእየተሰወሩ ይገኛሉ።\nየመንግስት የልማት\nተቋማት ክለቦች\nቁጥር እየቀነሰ\nየከነማ ክለቦች\nቁጥር እያበበ\nበሄደበት በዚህ\nዘመን የሸገር\nክለቦች አዲስ\nፈተና ለመጋፈጥ\nተገደዋል። ፕሪሚየር\nሊጉ ከተጀመረበት\n1990 ዓ.ም\nወዲህ እንኳን\nበአገራችን እግር\nኳስ ወጣቶችን\nበማፍራት ለብሔራዊ\nቡድኑ በመመገብ\nየሚታወቀው የሁለት\nጊዜ ቻምፒዮኑ\nመብራት ሃይል፣\nንግድ ባንክና\nመድንን የመሳሰሉት\nክለቦች ከሊጉ\nመውረድ ብቻ\nሳይሆን መፍረስም\nእጣ ፋንታቸው\nሲሆን ተመልክተናል።የከነማ ክለቦች ቁጥር መብዛት በመርህ ደረጃ መልካም መሆኑን በርካታ የስፖርት ቤተሰቦች የሚስማሙበት ቢሆንም የክለቦቹ የፋይናንስ አጠቃቀም በጤናማ መንገድ እስካልተጓዘ ድረስ የሚያስከትለው ውጤት የከፋ እንደሚሆን መገንዘብ ይቻላል። የከተማ ክለቦች የግብር ከፋዩን ህዝብ ገንዘብ በተጋነነ መጠን እግር ኳሱ ላይ ማፍሰሳቸው መሟላት ያለባቸው ብዙ ማህበራዊ አገልግሎቶችና ተንዶ የማያልቅ ችግሮች ላሉባቸው ከተሞች በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ነው። የፋይናንስ ጨዋነት ደንብ ባለመኖሩም የተጫዋቾች ደመወዝና የፊርማ ክፍያ ግሽበት ከስፖርትም የዘለለ ዓላማ ያነገቡትን አንዳንድ\nየክልል ክለቦች\nቅጥ ላጣ\nወጪና ብክነት\nአጋልጧቸዋል። ይህም\nበቀጥተኛነት በታክስ\nከፍዩ ህዝብ\nገንዘብ ላይ\nያልተንጠላጠሉትን ህዝባዊ\nየሆኑ እግር\nኳስ ክለቦችን\nለፈተና ዳርጓል።\nበተለይም ቅዱስ\nጊዮርጊስና ኢትዮጵያ\nቡና እንደ\nከነማ ክለቦች\nእጅግ ከፍተኛ\nዓመታዊ በጀት\nየመመደብ አቅምና\nእምነትም የላቸውም\nወይም አቅሙን\nእያጡ መጥተዋል።\nተጫዋቾች በሌሎች\nክለቦች ከፍ\nያለ ክፍያ\nየሚከፈላቸው መሆኑ\nእያደገ ከቀጠለ\nሁለቱን የሸገር\nክለቦች የመምረጥ\nዕድላቸው ጠባብ\nእየሆነ መሄዱ\nየግድ ነው።\nበዚሁ የክለቦቹ\nተፎካካሪነትም አብሮ\nመዳከሙን እንደሚቀጥል\nከወዲሁ አርቆ\nመመልከቱ አይከፋም።እንደ ኢትዮጵያ\nእግር ኳስ\nፌዴሬሽን የሪፎርም\nጥናት ከሆነ\nበፕሪምየር ሊጉ፣\nበከፍተኛ ሊግና\nበአንደኛ ሊግ\nእስከ ግንቦት\n30 ድረስ የመንግስት\nክለቦች የጨረሱት\nበጀት 2 ነጥብ\n2 ቢሊዮን ብር\nይደርሳል። እስከ\nሰኔ 30 ድረስ\nያለውን ጨምረን\nካሰላን ዘግናኝ\nውጤት እንደምናገኝ\nከግምት ይግባ።\nበፕሪምየር ሊጉ\nላይ የሚሳተፉ\nየከተማ ክለቦች\nዝቅተኛ ዓመታዊ\nበጀት የሚባለው\n58 ሚሊዮን ብር\nመሆኑን አንድ\nአንድ መረጃዎች\nይጠቁማሉ። የክልል\nከተማ ክለቦች\nአቅም እየፈረጠመ\nእግር ኳሱ\nላይ የሚያፈሱት\nመዋዕለ ንዋይ\nእየገዘፈ በሄደ\nቁጥር እንደ\nኢትዮጵያ ቡናና\nቅዱስ ጊዮርጊስ\nአይነት ህዝባዊ\nክለቦች ከዚህ\nበኋላ የዋንጫ\nተፎካካሪ የሚሆኑበት\nዘመን ቅርብ\nእንደማይሆን ብዙዎች\nምክኒያታዊ ስጋት\nአላቸው።ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተወዳዳሪ ክለቦች ብዛት ሲጀምርም ጥናት ያልተደረገበት መሆኑ እያደር በእያንዳንዱ ክለብና በአገራችን እግር ኳስ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን በማስረጃ መመልከት ይቻላል። የፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ክለቦች ብዛት ከ12 ወደ 14፣ ከ14 ወደ 16 ያደገበት አሳማኝ ምክንያት የለውም። የሊጉ ክለቦች ቁጥር 14 በነበረበት በ2004 ዓ.ም መቀመጫቸውን ሸገር ላይ ያደረጉ ክለቦች ብዛት ሰባት ነበር። በእርግጥ በዚያ ዘመን የሸገር ክለቦች የሊጉን እኩሌታ ቁጥር መያዛቸው በሌሎች የክልል ክለቦች ላይ የማይገባ የፉክክር ጥቅም ያስገኝላቸው እንደነበር መካድ አይቻልም። በሰንጠረዡ ግርጌ የጨረሰው ፊንጫ ስኳር በመኪና እየተዟዟረ ተዳክሞ ሲጫወት፣ ሰባቱ ክለቦች ብዙሃኑን የሊግ ጨዋታዎች ያለጉዞ ድካም በአዲስ አበባ ያካሂዱ ነበር። በዚያ ዓመት በሰንጠረዡ እስከ አራተኛ የነበረውን ቦታ ይዘው ያጠናቀቁት የአዲስ አበባ ክለቦች መሆናቸው አያስገርምም። የእግር ኳስ ተንታኙ ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ በማህበራዊ ድረ-ገፅ ይፋ ያደረገው ስታስቲክስ እንደሚጠቁመው በሊጉ በጨዋታ የሚቆጠረው አማካይ የጎል መጠን 2 ነጥብ 34 የነበረ ሲሆን እስካለንበትም 2011 ድረስ ይህን ያህል ጎል በአማካይ የተመዘገበበት ዓመት ከዚያ ወዲህ አልታየም። የዘንድሮው ደደቢት በደረሰበት ከባድ የፋይናንስ ችግር ምክንያት ስብስቡን በማሳሳቱ ዘንድሮ የሊጉ እጅግ ደካማው ቡድን በመሆን በዘጠኝ ዓመታት ከታየው ሁሉ መጥፎውን የጎል ዕዳ ይዞ ወርዷል። ይህም የሊጉን የጎል ብዛት ያለምክንያት አሳድጎታል። የ14\nክለቦች ሊግ\nከ16 ክለቦች\nሊግ የተሻለ\nመሆኑን ማየት\nተገቢ ነው።\n14 ክለቦች የሚፎካከሩበት\nሊግ በጨዋታዎች\nመካከል በቂ\nየማገገሚያ ጊዜ\nየሚሰጥ መርሐግብር\nስለነበር በንጽጽር\nያልተዳከሙ ተጫዋቾች\nበየጨዋታው የመገኘታቸው\nዕድል ከፍ\nያለ ሲሆን\nየጨዋታውም ግለት\nየተሻለ እንደሚሆን\nጥርጥር አይኖርም።\nበኢትዮጵያ የሊግ\nክለቦች ቁጥር\nየሚጨመርበትና የሚቀነስበት\nበጥናት የጎለበተ\nስፖርታዊ ምክንያት\nየለም። ሌላው\nቢቀር በዓመት\nየ58 ጨዋታ\nልዩነት ስለፈጠረ፣\nየኢትዮጵያ ጥሎ\nማለፍ ዋንጫ\nከሊጉ መርሃግብር\nጋር ተጣጥሞ\nየመከናወኛ ጊዜ\nበማጣቱ ለዛ\nቢስ እንዲሆን\nምክንያት መሆኑን\nማየት ይቻላል።የሊጉ ተወዳዳሪዎች\nብዛት በመደበኛነት\n16 ሲደረግ የሊጉ\nአማካይ የጎል\nመጠን እያሽቆለቆለ\nመጥቷል። በሊጉ\nየአዲስ አበባ\nክለቦች ብዛት\nበቀነሰ ቁጥር\nየቅዱስ ጊዮርጊስና\nኢትዮጵያ ቡና\nጎል የማስቆጠር\nአቅም እየወረደ\nሊሄድም ተገዷል።\nበስምንት ዓመት\nውስጥ የቅዱስ\nጊዮርጊስ የዓመቱ\nመጨረሻ የግብ\nክፍያ ከ39\nወደ 10 አሽቆልቁሏል።\nየሊጉ የጨዋታ\nአማካይ ጎል\nመጠንም ከ2004\nእስከ 2010 ባለው\nየጊዜ ርቀት\nበጨዋታ በአማካይ\nበ0 ነጥብ\n48 ጎል ቀንሷል።\nያለግብ የሚጠናቀቁ\nጨዋታዎች ብዛት\nእየጨመረ፣ የሊጉ\nአዝናኝነት እየቀነሰ\nሲመጣም ተስተውሏል።በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ቡና ጉዳይ ይበልጥ አስደንጋጭ ይመስላል። የሊጉ ቻምፒዮን ከሆነበት ከ2003 ወዲህ በየጨዋታው የሚሰበስበው አማካይ ነጥብ\nከ 2 ነጥብ\n1 ወደ 1 ነጥብ\n3 አሽቆልቁሏል። በሊጉ\nላይ ሰባት\nየአዲስ አበባ\nክለቦች በነበሩበት\n2003 እና ሶስት\nብቻ በቀሩበት\nበ2011 መካከል\nቡና በአማካይ\nበየጨዋታው የ\n0ነጥብ 8 ነጥብ\nማሽቆልቆል አሳይቷል።\nበተመሳሳይ በጎል\nመጠንም ቢሆን\nበሁለቱ ዘመናት\nመካከል በጨዋታ\n0 ነጥብ 8 ግብ\nቀንሷል። ሊጉ\nበዚሁ መልኩ\nከቀጠለ፣ ሁለት\nየሸገር ክለቦች\nብቻ በቀሩበት\nበ2012 የኢትዮጵያ\nቡና ዕጣ\nምን ይሆናል?\nየሚለውን ስንመለከት\nእውነትም አስደንጋጭ\nመሆኑን መረዳት\nይቻላል።የቅዱስ ጊዮርጊስም\nነገር እንዲሁ\nሳይታይ መታለፍ\nየለበትም። ከፍተኛ\nጎል ካስቆጠረበት\nከ2006 ወዲህ\nበአምስቱ ዓመታት\n‹‹የጎል ምርቱ››\nቀንሶበታል። ቢያንስ\nየ27 ጎሎች\nልዩነት አሳይቷል።\nይህ የሆነው\nበዘንድሮው ውድድር\n‹‹ፈረሰኞቹ ሶስት\nጨዋታዎችን ባለመጫወታቸው\nነው›› የሚል\nሙግት ሊነሳ\nይችላል። ነገር\nግን ሶስቱን\nጨዋታዎች ቢጫወቱና\nበእያንዳንዳቸው ስምንት፣\nስምንት ጎሎችን\nቢያስቆጥሩ እንኳን\nልዩነቱ የሚጠብ\nአይሆንም። በ2006\nአንድ ክለብ\n26 ጨዋታዎች ሲጫወት፣\n30 ጨዋታዎች ከሚያደርግበት\n2011 ጋር በአራት\nጨዋታ እንደሚያንስም\nልብ ማለት\nይገባል። የጨዋታዎች\nቁጥር በዝቶ\nየጎሉ መጠን\nይህን ያህል\nዝቅ የሚልበት\nአንድ አንገብጋቢ\nምክንያት ከሌለ\nበስተቀር በጤና\nእንዳልሆነ ግልጽ\nነው።ስፖርታዊ ባልሆኑ\nምክንያቶች በተለይ\nከሜዳ ውጭ\nተጉዞ ማሸነፍ\nብርቅ በሆነበት\nበዚህ ዘመን\n2012 ላይ የሊጉን\nባህሪ በአዎንታ\nየሚቀይር ሰማያዊ\nተዓምር ሊመጣ\nአይችልም። አካሄዱ\nሁሉ ነገር\nከድጡ ወደ\nማጡ እንደሚሆን\nምልክቶች መታየት\nከጀመሩ ሰነባብተዋል።\nጨዋነት የሚታይባቸው\nየክልል ክለቦች\nያሉ ቢሆንም፣\nበተጫዋቾች ላይ\nየስጋት ሸክም\nየሚጭኑ ስታዲየሞች\nየተበራከቱበት ሊግ\nላይ ተጫዋችም\nሆነ አርቢትር\nበሜዳ ላይ\nያለጭንቀት፣ በስፖርታዊ\nመንፈስ ውስጥ\nብቻ መቆየት\nአይችሉም። ክለቦቹ\nበራሳቸው ሜዳ\nእንደዕለቱ ብቃታቸው\nየላባቸውን የሚያገኙ\nከሆነና በክልል\nግጥሚያዎች ሆን\nብለው ለመሸነፍ\nየሚገደዱ ከሆነ\nከዚህ በኋላ\nየትኞቹም ክለቦች\nበልፋታቸው ልክ\nየዘሩትን ያጭዳሉ\nለማለት ይቸግራል።ይህም የከተማዋን\nክለቦች የፉክክር\nዕድል አደጋ\nላይ ይጥለዋል።\nበ2012 ከምንጊዜውም\nበበለጠ የሸገር\nክለቦች በጉዞ\nይደክማሉ፣ ከሜዳ\nውጪ ጨዋታዎቻቸው\nይበዛል። ከ2011\nይልቅ ወደ\nሶስት አዳዲስ\nየክልል ሜዳዎች\nተጉዘው የመጫወት\nግዴታ አለባቸው።\nበመከላከያ እግር\nኳስ ክለብ\nስንብት ምክንያት\nአዲስ አበባ\nበዓመት 30 ብቻ\nየሊግ ጨዋታዎች\nየሚደረጉባት ከተማ\nሆናለች። የከተማዋ\nክለቦች ከከተማዋ\nበራቁ ቁጥር\nደግሞ የሁለቱ\nአንጋፋ ክለቦች\nአሸናፊነት ዕድል\n(ስፖርታዊ በሆኑም\nይሁን ባልሆኑ\nምክንያቶች) እየቀነሰ\nመሄዱ አዲስ\nአበባን በእግር\nኳስ ቀጣይዋ\nድሬዳዋ ሊያደርጋት\nእንደሚችል ግልፅ\nይመስላል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 27/2011 ቦጋለ\nአበበ", "passage_id": "8d92ecf5b998ad44d0e102922b933bee" }, { "passage": "ትግራይ ስታዲየም\n\nበ2009 ዓ.ም በርካታ ቁጥር ያለው የስቴዲየም ብጥብጥ በተለይም በላይኛው ፕሪሚየር ሊግ ቢዘገብም ከብጥብጦቹ ጀርባ እግር ኳስን የሚሻገሩ ገፊ ምክንያቶች እምብዛም እንዳልነበሩ ይጠቀሳል።\n\nበያዝነው ዓመት በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚለኮሱ ግጭቶች እና ረብሻዎች ቁጥር አይሏል። \n\nከተጀመረ ጥቂት ሳምንታትን ብቻ ባስቆጠረው የ2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ከረብሻዎች ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በተለያዩ ክለቦች ላይ የጣለው ቅጣት ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደደረሰ ጉዳዩን የሚከታተሉ ባለሞያዎች ያስረዳሉ።\n\nመጠናቸው ይለያይ እንጅ ባለፉት ሁለት ወራት ሃዋሳ፣ ድሬዳዋ፣ አዲግራት፣ ጅማ እና በቅርቡ ደግሞ ወልዲያ ከተሞች ውስጥ ግጭቶች እና ረብሻዎችን አስተናግደዋል።\n\nባለፈው እሁድ በወልዲያ ስፖርት ክለብ እና በመቀሌ ከተማ መካከል ሊደረግ የነበረው የእግር ኳስ ጨዋታ ከመጀመሩ ከሰዓታት በፊት በሁለቱ ቡድኖች ደጋፊዎች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ህይወት የጠፋ ሲሆን ንብረት ላይ ዘረፋና ወድመት ተከስቷል።\n\nበዕለቱ ማገባደጃ ላይ በመቀሌ ከተማ መንገዶች ላይም ክስተቱን ለመቃወም በርካታ ሰዎች ወጥተው ነበር። ጨዋታው ካለመካሄዱ በተጨማሪ የግጭቱ አሻራ እስከቀጣይ ቀናት ቀጥሏል። \n\nየትግራይ ክልል የእግር ኳስ ፈዴሬሽንም ክስተቱን በማውገዝ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈደሬሽን ጉዳዩን ኣጣርቶ በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዲወስድ በደብዳቤ ጠይቋል።\n\nየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ባሻ የወልዲያው ክስተት ከእግር ኳስ የሚሻገር ገፅታ እንዳለው ይገልፃሉ።\n\nበሴካፋ ውድድር ከሚሳተፈው የወንድ አዋቂዎች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ጋር ናይሮቢ የሚገኙት አቶ ጁነዲን ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ግጭቱ ከስፖርት ሜዳ ውጭ መቀስቀሱን አስታውሰው \"ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ይዘት ያለው ነገር ነው። ሜዳ ውስጥ ቢሆን ከኳስ ድጋፍ ጋር ይያያዝ ነበር፤ ሌላ ትኩሳት ያለበት ነው የሚመስለኝ፤ እግር ኳስ ብቻውን አይመስለኝም\" ሲሉ ተናግረዋል።\n\nከማኅበረሰባዊነት እስከ ብሔረተኛነት\n\nበስፖርቱ ዓለም የተመልካቾች ነውጠኛነት ምክንያቶች ብዙ ናቸው ሲል የሚያስረዳው የስፖርት ተንታኙ መንሱር አብዱልቀኒ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ ወይንም ምጣኔ ኃብታዊ ብሶቶች ስቴዲየም ላይ ሊያጠሉ እንደሚችሉ ይናገራል። \n\nበኢትዮጵያ እግር ኳስን የታከከ ብጥብጥ ሲከሰት \"የመጀመሪያው ባይሆንም እየተባባሰ ግን ሄዷል። የቅርብ ጊዜ ክስተቶችን ስናጤን ደግሞ ከእግር ኳስ ባሻገር ሌሎች የጀርባ ምክንያቶች እንዳሉ ግልፅ ነው\"ይላል።\n\nእግር ኳስ ማኅበረሰባዊ መሰረት ከሌለው በስተቀር የጠነከረ የእኔነት ስሜት ሊፈጥር አይቻለውም የሚለው መንሱር፤ ይሁንና ክለቦች ከማኅበረሰባዊ መሰረታቸው በዘለለ ብሔር ተኮር መልክን እየተላበሱ የመምጣታቸውን አዝማሚያ \"አደገኛ ነው\" ይለዋል።\n\n\"ከአንዳንድ በጥባጭነት እጅግ ወደተደራጀ ነውጠኛነት ሊሄድ ይችላል። ቀስ በቀስ ወደመቧደን እየተሄደ ነው። ራሳችንን መከላከል እና ማዘጋጀት አለብን በሚል ደጋፊዎች ራሳቸውን ማደራጀት ከጀመሩ የሚያሰጋ ዓይነት እውነታ ሊፈጠር ይችላል።\"\n\nላለፉት ሁለት ዓመታት መቀሌ ከተማ የእግር ኳስ ክለብን የደገፈውና ባለፈው እሁድ ማለዳ የወልዲያ አመሻሹን ደግሞ የመቀሌ ኹከቶችን የታዘበው ገብረመድህን ኃይለስላሴ በዚህ አስተያየት ይስማማል።\n\n\"የእኔነቱ መንፈስ ከርሮ ከኳስ ወዳጅነት ወደብሔርተኝነት ነው እየሄደ ያለው፤ ከዚህ ቀደም ብጥብጡ ተጀምሮ የሚያልቀው ስቴዲየም ነው፤ ከዚያ አያልፍም። አሁን አሁን እየታየ ያለው ግን የባሰ ነው\" ሲል ለቢቢሲ አስተያየቱን ሰጥቷል።\n\nየፋሲል ከነማ የእግር ኳስ ክለብን የሚደግፈውና የድጋፍ እንቅስቃሴዎችን... ", "passage_id": "6439fb0061a049795c4a01718f0e6d35" }, { "passage": "ስለ ኢትዮጵያ ማወቅ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ሰነዶችን ቢበረብር፣ መረጃዎችን ቢያገላብጥ፣ ወይም በይነ መረቦችን ቢያስስ ከተፈጥሮና ሰው መሰራሽ ሀብቶቿ መካከል አንዱ አትሌቲክስ መሆኑን ይገነዘባል። ኢትዮጵያ በዓለም ሕዝብ ዘንድ ከእውቅናም በላይ ከበሬታን እንድታገኝ ካደረጉ ጉዳዮች መካከል በኦሊምፒክ ማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቀ የመጀመሪያው ጥቁር አትሌት የአበበ ቢቂላ አገር መሆኗ ትልቅ ድርሻ አለው። መረጃዎች አበበ ቢቂላ በባዶ እግሩን ሮጦ ከማሸነፉም በላይ ከአራት ዓመታት በኋላም ከዓለም ክብረወሰን ጋር ድርብ ድል መቀዳጀቱን ሳያስታውሱ አያልፉም። ስፖርቱን፣ አሸናፊነቱንና ክብሩን ትውልድ እየተቀባበለ ለዘመናት ማኖሩም በወርቅ ቀለም የተጻፈ የታሪክ አካል ነው። አትሌቲክስ ለኢትዮጵያ በቻምፒዮናዎች እና የኦሊምፒክ መድረኮች ላይ በመም፣ በጎዳና ወይም በሀገር አቋራጭ ውድድር ሜዳሊያ የምታስመዘግብበት ዘርፍ ብቻም አይደለም። ከኩራትና የአንድነት ስሜት ምንጭነቱ ባሻገር ሀገር ትለማና ትበለጽግ ዘንድ የበኩሉን በማድረግ እየተረባረበ ነው። ብርቅየ አትሌቶች በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ፤ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት፣ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ፣ በአግሮ ኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽን፣ በአውቶሞቲቭና በመሳሰሉት ዘርፎች በመግባት ለወጣቱ የስራ እድል በመፍጠር ረገድ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። ስፖርቱ መዋዕለ ንዋዩን በማፍሰስ የድርሻውን ከመወጣት ባለፈም ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይም ቅድሚያና ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆኑም እሙን ነው። በተለያዩ ጊዜያት በፌዴሬሽኑ፣ በአትሌቶችና በሙያ ማህበራት በተናጠልና በቡድን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለማውሳትም፤ ከወቅታዊው የኮሮና ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተከናወነውን ስራ በምሳሌትነት ማንሳት ይቻላል። የገንዘብና የቁሳቁሰ ድጋፍ ከማድረግም ባለፈ በማዕድ ማጋራት ላይም ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት ችሏል። አሁንም መንግስት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታና የውሃ ሙሌት ላይ የያዘውን አቋም በጽኑ እንደሚደግፍ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ግንባታው እስኪጠናቀቅ ድረስም የአትሌቲክስ ቤተሰቡ ከመንግስትና ከህዝብ ጎን የሚቆም መሆኑንም በድረገጹ ባወጣው መግለጫ አስነብቧል። ለረጅም ዓመታት ሲጓተት የቆየው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሂደቱ እየተፋጠነና የውሃ ሙሌቱም በተያዘው\nክረምት  የሚጀመር መሆኑን መንግስት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ነው ፌዴሬሽኑ የድጋፍ መግለጫውን ያወጣው። በዚህም የፌዴሬሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች፣ አትሌቶች፣ የአትሌት ተወካዮችና አሰልጣኞች፣ የአትሌቲክስ ዳኞች እንዲሁም በስፖርት ቤተሰቡ በቁርጠኝነት እንደሚደግፍ ጠቁሟል። ፌዴሬሽኑ ከዚህ ቀደም ቦንድ በመግዛትና ድጋፍ በማሰባሰብ፣ ከዚሁ ጎን ለጎን የፌዴሬሽኑ አመራሮችና የአትሌቲክሱ ቤተሰብ በስፍራው በመገኘት ግንባታውን መመልከቱ ይታወሳል። ከ40ሺ በላይ ሯጮችን ያሳተፉ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮችን በማካሄድም የግድቡን ግንባታ የሚደግፉ አካላትን የማነቃቃት ስራም አከናውኗል። በቅርቡም ፌዴሬሽኑ ለሕዳሴው\nግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ\nጽህፈት ቤት የገንዘብ\nድጋፍ አበርክቷል። አባይና የህዳሴ ግድቡ ለአትሌቶችና የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንደማንኛውም\nየህብረተሰብ ክፍል የህልውና\nጥያቄ በመሆኑም በአካል በቦታው  በመገኘት፣ ለግንባታው በማስተባበር፣ አቅም የፈቀደውን የገንዘብ አስተዋጽኦ በማድረግ እንዲሁም በግልና በቡድን ለግንባታው የሚያግዙ የዲፕሎማሲ ስራዎችም በተጨማሪነት እየተሰሩ እንደሚገኙም በመግለጫው ተመልክተዋል። ይህ ሂደት የአንድ ወቅት ብቻ ባለመሆኑ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ድጋፉን አጠናክሮ በመቀጠል፤ ስራው እንደ ድል አድራጊ አትሌቶች በጽናትና በቁርጠኝነት እንደሚጠናቀቅም እምነት ተጥሎበታል። ፌዴሬሽኑ ከግድቡ ባሻገር የደም ልገሳና አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የችግኝ ተከላ በቅርቡ ለማካሄድም በዝግጅት\nላይ ይገኛል። በዓለምና\nሀገር አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ በሚገኘው\nየኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ\n(ኮቪድ 19) ምክንያት እየተከሰተ\nያለውን የደም እጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት የደም ልገሳ መርሃ ግብር በማዘጋጀት\nፌዴሬሽኑ ለስፖርቱ ቤተሰቦች\nጥሪ አድርጓል። በቀጣይ ሳምንት ሰኔ  16/2012 ዓም ከማለዳው ሶስት ሰዓት ጀምሮ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቢሮ ሰራተኞች፣ አንጋፋ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ የአትሌት ተወካይ ማናጀሮች፣ ሁሉም የአትሌቲክስ ማህበራት አመራሮች፣ የክለብ አመራሮች በአጠቃላይ የአትሌቲክሱ ቤተሰብ በፌዴሬሽኑ አስተባባሪነት የደም ልገሳውን ለማካሄድ ቀጠሮ ይዛል። ፌዴሬሽኑ ከኢትዮጵያ ደም ባንክ አገልግሎት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ታሪካዊና አገራዊ ጉዳይ ላይ ሁሉም የድርሻውን እንዲያበረክትም ጥሪውን አስተላልፏል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተመናመነ ያለውን የሀገሪቷን የደን ሽፋን እንዲያገግም ለማድረግም ከመንግስት ጎን በመቆም የአረንጓዴ አሻራን በችግኝ ተከላ ለማሳረፍም እቅድ ይዟል። የአትሌቶች የህይወት ምንጭ የሆኑትን የዛፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የትና መቼ እንደሚከናወን በቅርቡ እንደሚያሳውቅም ጠቁሟል።  አዲስ ዘመን ሰኔ10/2012ብርሃን ፈይሳ ", "passage_id": "d8d94b43638fd2e8af912cafe5230dad" }, { "passage": "አካዳሚዎች የሁሉም ስፖርቶች መሠረት ለመሆናቸው ዓለም አቀፍ ልምዶችን መመልከት በቂ ነው። በስፖርቱ መሠረት ያላቸውን ታዳጊዎች ሰብሳቢ የሆኑት አካዳሚዎች ድንቅ የእግር ኳስ፣ አትሌቲክስ፣ ብስክሌት፣ ቦክስ ወዘተ…ጥበበኞች በማፍራት ረገድ ስኬታማ መሆናቸው የአደባባይ ምስጢር ነው። በአካዳሚዎች ገና ከሕፃንነታቸው እንዲሰለጥኑ መንገድ በመክፈት፤ ወደ ታዳጊነት በማሸጋገር ራዕያቸውን እንዲያሳኩ በማንደርደርና ወደ ታላቅነት ስፍራ በማድረስ ይሄንኑ አስመስክረዋል። በዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች ስኬታማ መሆን የቻሉ ስፖርተኞች መነሻቸው ሲፈተሽ በዚህ መንገድ የተጓዙ ሆነው እናገኛለን። የአካዳሚውን መሠረታዊ ጥቅም የተረዱ እንደነ እንግሊዝ፣ ስፔን ወዘተ… በተለይ በእግር ኳሱ ላይ ትኩረት አድርገው ሰርተዋል። ውጤታማ ለመሆንም መብቃታቸው በዘርፉ የተደረጉ ጥናቶች ምስክር ሆነው ይቀርባሉ። ከዚህ አኳያ አካዳሚዎችን ወደ አገራችን ማምጣቱ ለስፖርቱ ትንሳኤ ዋነኛው መድህን እንደሚሆን በስፖርት አዋቂዎች በኩል ሲንጸባረቅ ቆይቷል። ምክረ ሃሳብ ተደጋግሞ በስፋት ተነግሯል። በተለይ ደግሞ፤ ኢትዮጵያ በዓለም ታላላቅ መድረኮች የታወቀችበትን አትሌቲክስ ስፖርት በመጥቀስ፤ ከዓለም በ5 ሺ ፣10 ሺ ሜትር እንዲሁም በማራቶን ስሟ በቀዳሚነት ትጠራለች።ከዚህ ጥሪ ፊት ለፊት ሞገስ ሆነው የሚቀርቡት ደግሞ ጀግኖች አትሌቶቻችን ናቸው። የአትሌቶቹ ስኬታማነት በግላቸው የሚያደርጉት ጥረትና ከአሰልጣኞቻቸው የሚቸራቸውን ሙያዊ እገዛ ምርኩዝ በማድረግ ነበር። የተፈጥሮ ችሎታቸውን መሠረት ባደረገ ሁኔታ በሳይንሳዊ ሥልጠና ባልታገዙበት በዚያን ዘመን፤ በፍላጎትና በአገር ፍቅር ለድል በቅተዋል። የትናንት ጀግኖች አትሌቶቻችን ከተፈጥሯዊ ችሮታቸው ጋር ሳይንሳዊ ሥልጠናው ቢደመር ምናልባትም ከሰሩት ታሪክ የበለጠ እንደሚሰሩ ጥርጥር የለውም። በአካዳሚዎች መሠረት ባለው ሁኔታ በአትሌቲክሱ ያለውን የተፈጥሮ ችሮታ ደግፎና አሳድጎ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ በስፖርት አዋቂዎች በኩል ተደጋግሞ ሃሳብ ሲቀርብ ቆይቷል። መንግሥት ምክረ ሃሳቡን «ጆሮ ዳባ ልበስ» በሚል አንጥሮ በመመለስ ዓመታትን ተጉዟል። አትሌቲክስን ጨምሮ በተለያዩ የስፖርቱ ዓይነቶች እየተስተዋለ ያለው የውጤት መዋዠቅ ብሎም፤ አንጋፋዎቹን የሚተኩ ታዳጊዎች አለመኖር አካዳሚዎችን ማቋቋሙ መሠረታዊ መፍትሄ እንደሆነ አቋም እንዲያዝ አድርጓል።ስፖርቱን በሚመራው ኮሚሽን ዘንድ ሃሳቡን በመግዛት ወደ ትግበራ ለመቀየር በቅቷል። በዚህም መሠረት ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ በማድረግ በወጣቶች ተስፋ ሰንቆ የኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት አካዳሚ ተቋቋመ። መንግሥት የአካዳሚው መቋቋም ፋይዳው ዘግይቶ ቢገባውም፤ ወደ ትግበራው መግባቱ እንደመልካም የተቆጠረለት ነበር። ይሄንን መስመር በማለፍ አካዳሚው በ2005 ተመርቆ በ2006 ዓ.ም ስፖርተኞችን መልምሎ ሥራውን ጀምሯል። በአትሌቲክስ፣ በፓራሊምፒክ፣ በቮሊቦል፣ በእግር ኳስ፣ በውኃ ዋና፣ በወርልድ ቴኳንዶ፣ በቅርጫት ኳስ፣ በጠረጴዛ ቴኒስ፣ በቦክስና በብስክሌት የስፖርት ዓይነቶች ሥልጠና በመስጠት ጉዞውን ሊጀምር በቅቷል። አካዳሚው የሥልጠና አቅሙን ከፍ ለማድረግ በ2002 ዓ᎐ም ሥራ ከጀመረው የጥሩነሽ ዲባባ ማሰልጠኛ ማዕከልን በመጠቅለል ትግበራውን አጠነከረ። የኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት አካዳሚ በአዲስ አበባ ካምፓስ በሀገሪቱ ስፖርት የሚስተዋለውን የተተኪ ችግርን ሳይንሳዊ በሆነ ሥልጠና ታግዞ ለመቅረፍ ወደ ትግበራ ከገባ አምስት ዓመታትን አስቆጥሯል። አካዳሚው በአምስት ዓመት ቆይታው ያስመዘገበውን ውጤት፣ የነበሩበትን ተግዳሮቶችንና ቀጣይ ለመጓዝ ያሰበውን አቅጣጫ በተመለከተ በጥቅምት 14 ቀን 2012 ዓ.ም በአካዳሚው መሰብሰቢያ አዳራሽ ለጋዜጠኞች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል። የአካዳሚው ዋና ዳይሬክተር አቶ አንበሳው እንየው እንደገለፁት፤ የአካዳሚው አላማ የታዳጊዎችና ወጣቶች ሥልጠና አደረጃጀት እና አሠራር ከልማዳዊ አሠራር በማላቀቅ ሳይንሳዊ ዘዴ ላይ እንዲመሰረት ማድረግ ነው። ስፖርቱን ወደ ተሻለ አድማስ ለማድረስ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ ታዳጊዎችን በ10 የስፖርት ዓይነቶች በመመልመል አሰልጥኖ ማስመርቁን ይገልጻሉ። አካዳሚው ምርጥ ስፖርተኞች የማፍራት ተልዕኮውን በመያዝ ከአምስት ዓመት በፊት መቋቋሙን አስታውሰውም፣ ከ2009 ዓ.ም እስከ 2011 ዓ.ም በሦስት ዙር ያሰለጠናቸው 181 ስፖርተኞች 140\nየተለያዩ ክለቦችን እንደተቀላቀሉ አብራርተዋል። በዚህም አካዳሚው ተልዕኮው ከማሳካት አኳያ እየተሳካለት እንደሚገኝ ይናገራሉ።እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ ፤አካዳሚው ባለፉት አምስት ዓመታት በነበረው ጉዞ በጥንካሬ በርካታ ነጥቦችን አንስቷል። የመጀመሪያው ሰልጣኞች በአካዳሚው በሥልጠና ላይ እያሉ በክለቦች መመረጣቸው ነው። በተናጠልም በቡድን አገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውጤቶች ማስመዝገባቸው ሌላኛው ጥንካሬ ነው። ሰልጣኞች በስፖርት ሥልጠና የተለያዩ ክህሎቶች እንዲሁም በአካዳሚክ እና ተጨማሪ የቋንቋ እና የመሠረታዊ ኮምፒዩተር ክህሎት እንዲይዙ መደረጉ እና በተለያዩ ምክንያት በውድድር ስፖርት መቀጠል ያልቻሉ በተጓዳኝ ሙያዎች (በአሰልጣኝነት አልያም በዳኝነት መቀጠራቸው) እንደ ጥንካሬ ተነስቷል።ሰልጣኞቹ ከተመረቁ በኋላ እያደረጉ የሚገኘውን እንቅስቃሴና ያመጡትን ውጤት ምን እንደሚመስል ዳሰሳ ማድረግ እንደተቻለ የተገለፀ ሲሆን እንደ ጥንካሬም ተወስዷል። የአካዳሚው ቆይታቸውን የጨረሱ ሰልጣኞች የሙያ ብቃት ምዘና ሲኦሲ እንዲወስዱ የሚደረግ መሆኑ ሰልጣኞቹ በአቅም፣ ችሎታና እውቀት ምልኡ በመሆን እንዲወጡ ማድረጉም ተቀምጧል። በሦስት ዙር ተመርቀው ከወጡ ስፖርተኞች የሙያ ብቃት ምዘናውን ከወሰዱት 99 በመቶ ያህሉ ያለፉ ናቸው። ይህም በአካዳሚው የሚሰጠው ሥልጠና ፍሬያማ መሆኑን ያስገነዘበ ጭምር መሆኑን በጥንካሬ ታይቷል። በተጨማሪም ሰልጣኞች የመደበኛ ትምህርት ፍላጎት እያደገ መምጣቱ በመልካም ጎኑ የተገለጸ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከአካዳሚው የሚወጡ ስፖርተኞቸ በስፖርተኞቹ ብቻም ሳይሆን በመደበኛውም ትምህርት የተሻሉ እንዲሆኑ የሚያግዝ ተሞክሮ መሆኑን ነው ያብራሩት። የአካዳሚው ትምህርትና ሥልጠና ውድድር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብዮት ተስፋዬ፤ የአካዳሚው ፍሬዎች በ2011 ዓ.ም በነበሩ አህጉር አቀፍና ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች በመሳተፍ የነበራቸውን ውጤታማነት ለአካዳሚው ስኬት እንደማሳያ አንስተዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያ ውጤታማ ያልነበረችበት ርቀት ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል ቢሆንም አሁን ታሪክ ተቀይሯል። በራባት ሞሮኮ በተካሄደው የመላ አፍሪካ ጨዋታና የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ የሆነው የኢትዮጵያ የርቀቱ ባለ ክብረ ወሰን ጌትነት ዋለ አካዳሚው ካፈራቸው ስኬታማ አትሌቶች ዋነኛው መሆኑን ነው ያመላከቱት። ቦነስ አይረስ ላይ በተካሄደው የዓለም የታዳጊዎች ኦሊምፒክ የወርቅ ባለቤት የሆነው አብርሃም ስሜ፣ በማራካሽ ሞሮኮ በተካሄደው 4ኛው ኢንተርናሽናል ፓራሊምፒክ አትሌቲክስ ውድድር በ1 ሺ500 ሜትር ወርቅ፣ በ800 ሜትር ነሐስ ሜዳሊያ ማስመዝገብ የቻለው ገመቹ አመኑ እንዲሁም በተመሳሳይ መድረክ በ200 ሜትር እና በ400 ሜትር ወርቅ ያስመዘገበችው ዝናሽ አሰፋ የአካዳሚው ስኬታማነት ማሳያ መሆናቸው ይገልጻሉ። በዓለም አቀፍና በአህጉር አቀፍ መድረኮች የአካዳሚው ፍሬ የሆኑ ስፖርተኞች እያስመዘገቡ የሚገኙት ውጤት አካዳሚው ከተቋቋመበት አላማና ራዕይ እኩል እየተጓዘ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ አስቀምጠዋል:: አካዳሚው የቆመለትን ዓላማ አጠናክሮ ለማስቀጠል ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ የሁለተኛ ዘመን ስትራቴጂክ እቅድ ዝግጅት ትግበራ በሕዝብ እና አጋሮች ተሳትፎ እንዲከናወን የሚያስችል ሥራ የሚሰራ መሆኑንም ነው ያብራሩት። አዲስ ዘመን ጥቅምት 16/2012 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "6341bc919ff668d2332502bab8dda291" } ]
a4634985fc9834dce40302640ba07231
c90adf0b7116e3eb91ba588d29379983
«ሀገራችንን እየተፈታተናት ያለው ዓይነ ሥውርነት ሳይሆን የልብ ሥውርነት ነው” – ዶክተር ሙሉነሽ አበበ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- «ሀገራችንን እየተፈታተናት ያለው ዓይነ ሥውርነት ሳይሆን የልብ ሥውርነት ነው» ሲሉ በአማራ ክልላዊ መንግሥት ምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የአማራ ክልል ሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሙሉነሽ አበበ ተናገሩ። «አካል ጉዳተኞችን አካታች፣ ምቹ እና ዘላቂ የተሻለ ዓለምን በድኅረ ኮቪድ 19 እንገንባ» በሚል መሪ ሐሳብ የአካል ጉዳተኞች ቀን በዓለም ለ29ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ28ኛ ጊዜ በባሕር ዳር ከተማ በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል።የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ መረጃ እንደሚያመለክተው ዶክተር ሙሉነሽ በበዓሉ ሥነሥርዓት ወቅት እንደተናገሩት፤ አካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታ ከተፈጠረላቸው ሙሉ አካል እንዳላቸው ሰዎች እኩል ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ መሥራት ይችላሉ። ለዚህም በርካታ ምስክሮች አሉ። ዋናው ጉዳይ ግን ሀገራችንን እየተፈታተናት ያለው ዓይነ ሥውርነት ሳይሆን የልብ ሥውርነት ነው። ልባቸው የተሠወሩት እኩያን ከሰው ስብእና ውጪ በመሆን ወገኖቻችንን በአሰቃቂ ሁኔታ እየጨፈጨፉ ይገኛሉ። በመሆኑም ከዚህ መጥፎ ተግባር ለመውጣት ሁሉም ቆም ብሎ ማሰብ ይጠበቅበታል።የፌዴራል ሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ለዓለማችን ታላላቅ አስተዋጽኦ አበርክተው ያለፉ አካል ጉዳተኞች ስማቸው ከመቃብር በላይ ሆኖ ሁሌም ሲዘከሩ ይኖራሉ። ለሀገራችንም እድገት እና ብልጽግና አስተዋጽኦ እያደረጉ የሚገኙ በርካታ አካል ጉዳተኞች አሉ። በመሆኑም አካል ጉዳተኞች ጠንክራችሁ ከሠራችሁ «ለሀገራችን ጠቃሚ እንጂ ተጠቃሚ አንሆንም» የሚለውን አስተሳሰብ መያዝ ይገባል። በሀገራችን የአካል ጉዳተኞች አስገዳጅ ሕግ አልነበረም፤ በዚህ ዓመት ግን የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ ሥራ ላይ ይውላል፤ ይህም መንግሥት ለአካል ጉዳተኞች ትኩረት መስጠቱን ያመላክታል።የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማኅበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዓባይነህ ጉጆ በበኩላቸው፣ የበዓሉ ተቀዳሚ ዓላማ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአካል ጉዳተኞች ዙሪያ ያለውን የተዛባ አስተሳሰብ ግንዛቤ ፈጥሮ ማስተካከል መሆኑን ጠቁመው፣ ፌዴሬሽኑም የመንግሥት አካላት ስለአካል ጉዳተኞች ግንዛቤ ኖሯቸው በትምህርት፣ በጤና፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በፖለቲካ እና በማኅበራዊ ተግባራት አካትተው እንዲሠሩ የግንዛቤ ፈጠራ እየሠራ ነው።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38342
[ { "passage": "አዲስ አበባ ባለፈው ሳምንት ለየት ያለች አዲስ ጋዜጣ አግኝታለች። ጋዜጣዋ ለዓይነ ስውራን ተብላ የተዘጋጀች [በዳሰሳ የምትነበብ] በብሬል የተጻፈች ስትሆን \"ፈትል\" ትሰኛለች።ጋዜጣዋን በባለቤትነት የምታሳትመው ደግሞ ፊዮሪ ተወልደ ስትሆን፤ የአንዷ ጋዜጣ የመሸጫ ዋጋ 30 ብር መተመኑን ትናገራለች።የጋዜጣዋን ሃሳብ የአካል ጉዳተኞች ማኅበራት ፌዴሬሽን እንዲሁም የዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበራት መደገፋቸውን ፊዮሪ ለቢቢሲ ተናግራለች።የጋዜጣዋ የመጀመሪያ ህትመት ባለፈው ሳምንት ለመንግሥት ተቋማትና ለዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበሩ ቅርንጫፍ ቢሮዎች ለማስተዋወቅ በሚል ተሰራጭቷል።ፊዮሪ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ህትመት ውጤት በሆነው ዕለታዊው የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ በጋዜጠኝነት ትሰራ ነበር። አሁን ደግሞ ባዜን የማስታወቂያና ህትመትና ፕሮሞሽን የተሰኘ ድርጅት አቋቁማ \"ፈትል\" የተሰኘችውን ጋዜጣ ለዓይነ ስውራን ማሳተም ጀምራለች።ይህችን አዲስና ለየት ያለች ጋዜጣን ለማዘጋጀት ምክንያት የሆናት ቀደም ሲል አራት ኪሎ ወደ ሚገኘው መሥሪያ ቤቷ በመትሄድበት ጊዜ የምትመለከተው ነገር እንደሆነ ታስታውሳለች። ፊዮሪ፣ በዚያ ወቅት ዘወትር ወደ ሥራ ገበታዋ በምታቀናበት ወቅት አራት ኪሎ አካባቢ በሚገኙት ካፌዎች ውስጥ ጋዜጣ ይዘው፣ የሚጠጡትን ትኩስ ነገር በማዘዝ የሚያነብቡ ሰዎችን ስትመለከት በውስጧ ጥያቄን ያጭርባታል። እነዚህ በየዕለቱ የተለያዩ ጋዜጦችን ገጽ የሚያገላብጡ ሰዎች በአገራቸው በዚትዮጵያ ውስጥ እንደሁም በመላው ዓለም ስለተከሰቱ ነገሮች ዜና ፈልገው ብቻ ሳይሆን የሥራ ማስታወቂያም ለመመልከት ነው። ታዲያ ይህንን ዕድል ያላገኙት የኅብረተሰቡ ክፍሎች ነገር ያሳስውባት ነበር። \"በተለይ ደግሞ ዓይነ ስውራን ይህን እድል ተነፍገዋል\" ትላለች ፊዮሪ። ስለዚህም እንደ ጋዜጠኛ እድሉን ላላገኙ ሰዎች በቻለችው አቅም እድሉን የማመቻቸት ኃላፊነት እንዳለባት በማመን ለዓይነ ስውራን የሚሆን ጋዜጣን ለማዘጋጀት እንደተነሳች ትናገራለች።ስለዚህ ጋዜጣው ለዓይነ ስውራን መረጃ ብቻ እንዲያደርስ አልፈለገችም፤ የሥራ እንዲሁም የጨረታ ማስታወቂያዎችን ይዞ ዓይነ ስውራን በአገሪቱ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ በመረጃ የታገዘና የተጠናከረ እንዲሆን አስተዋጽኦ ለማበርከት በማሰብ ሥራውን ጀመረች።ፈትል የተሰኘችው ጋዜጣዋም ዜናና መረጃዎችን ከማቅረብ ባሻገር ለዓይነ ስውራን \"የኢኮኖሚ ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥም\" የራሷ አስተዋጽኦ እንደሚኖራት ትናገራለች።በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ወደ አራት ሚሊዮን ዓይነ ስውራን ይኖራሉ ተብሎ ይገመታል። ከእነዚህ ግለሰቦች መካከል ማየት ብቻ ሳይሆን የመስማት ችግርም ያለባቸው ስላሉ በሬዲዮና በቴሌቪዥን የሚተላለፉ መረጃዎችን አፍ ተልብ ሆኖ ለመከታተል እድሉን ላያገኙ ይችላሉ።ስለዚህ እንደ ጋዜጠኛዋ ፊዮሪ ገለጻ \"እነዚህን ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸው ዜጎች በብሬል ጋዜጣ የመረጃ ተጠቃሚ ማድረግ ችላ ተብሎ ሊታለፍ የሚገባው እድል አይደለም።\"ጋዜጣው ልክ እንደሌሎቹ አቻዎቹ ሁሉ የተለያዩ አምዶችን ይዟል።ዜና ቀዳሚው ነው፣ ከአይነ ስውራን ጋር በተያያዘ የሚደርሱ የፍትህ መዛባትና መጓደልን በምርመራ ዘገባ የሚያቀርብበት፤ ፈትል ነቃሽ፣ እንግዳ፣ ተምሳሌትና የመሳሰሉ ሁሉን አቀፍ መረጃዎች የሚቀርቡበት ነው። ከእነዚህ በተጨማሪ ደግሞ ዓይነ ስውር ልጆችን ለመድረስ በማሰብ የልጆች አምድ በጋዜጣዋ ውስጥ ተካቷል። ጋዜጣዋ የምታተመው በኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማህበር በኩል መሆኑንም ፊዮሪ ተናግራለች።መደበኛ ጋዜጦች ዘወትር ለሥራቸው ፈተና የሆነባቸው እየጨመረ የሚሄድ የወረቀት ዋጋ መወደድ የዓይነ ስውራኑ ጋዜጣ የሆነችው የ\"ፈትል\"ም ፈተና ነው።የብሬል ወረቀት በአገር ውስጥ ገበያ ላይ እጅግ ውድ መሆኑን የምትጠቅሰው ፊዮሪ፤ ነገር ግን የጋዜጣዋ መሸጫ ዋጋ ለህትመትና ለወረቀት መግዣ ከሚወጣበት በእጅጉ አንሶ ለገበያ እንደቀረበች ትናገራለች። ሌላው አብዛኞቹ ዓይነ ስውራን የኢኮኖሚ አቅማቸው አነስ ያለ መሆኑ ጋዜጣዋን በመደበኛው ገበያ ውስጥ አቅርቦ በመሸጥ ስርጭቱን ለማስፋት ተግዳሮት እንዳለባት ጠቅሳለች። ጋዜጣዋን ለማስተዋወቅና ለዓይነ ስውራን ተደራሽ ለማድረግ አሁን እንደ መፍትሄ ብለው ያስቀመጡት፤ የመጀመሪያው የጋዜጣዋ ዕትም ስርጭት ትምህርት ቤቶች ሲከፈቱ በአገሪቱ በሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ እንዲሆን ታስቦ ነው። በተጨማሪም የመንግሥት ተቋማት፣ የዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበሩ ዋና ቢሮ እና ቅርንጫፍ ቢሮዎች እንዲሁም ትልልቅ ጋዜጣ የሚሸጥባቸው አደባባዮች ላይ \"ፈትል\"ን ለማከፋፈል ማሰቧን ትናገራለች።የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለዓይነ ስውራን ተማሪዎቻቸውና መምህራኖቻቸው በመግዛት በቢሮዎችና በቤተ መጻህፍት እንዲያስቀምጡላቸው ለመስራት በማሰብ ጥረት መጀመሯንም ገልጻለች። \"ፈትል\" ሳምንታዊ የዓይነ ስርውራን የብሬል ጋዜጣ በአሁኑ ጊዜ በአማርኛ ብቻ የምትታተም ሲሆን በቀጣይ በሌሎች የአገሪቱ ቋንቋዎችም የማዘጋጀት ሃሳብ መኖሩንም አዘጋጇ ፊዮሪና ተወልደ ጠቁማለች።", "passage_id": "ee8cd6edd759dbac93a83f5f2d699c1c" }, { "passage": "እቴጌ፡ የጡት ካንሰርን በቀላሉ በስልክዎ መለየት እንደሚችሉ ያውቃሉ?\\nየሕክምና ባለሙያ ከሆኑት አባቷና ከሥነ-ሕንፃ ባለሙያ እናቷ አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዳ ያደገችው ቤተል የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ናዝሬት ስኩል ነው የተከታተለችው።\n\nለኔም ሆነ ለወንድሜ ሕክምና ማጥናት የቤተሰቦቼ አስተዋጽኦ ቀላል አይደለም የምትለው ቤተል፣ በናዝሬት ስኩል ስትማር በሴቶች ላይ የሚሠሩ ሥራዎች ላይ እንዳታተኩር የሚያስችላትን ምክር ከመምህራኖቿ ተቀብላለች።\n\n\"ሴቶች ትምህርት ቤት መማሬ...\" ትላለች ቤተል፣ \"...ሁል ጊዜ የሚነገረን እኛ ዕድለኛ መሆናችንና በርካታ ሴቶች እኛ ያገኘነውን እድል ስለማያገኙ የሴቶችን ሕይወት ለመለወጥና ለማሻሻል መሥራት እንዳለብን ነበር።\" \n\nየሕክምና ተማሪዎች ማሕበር ውስጥ ከገባች በኋላ የበጎ አድራጎት ሥራ አልያም የሕክምና ትምህርቱን ለማዘመን፣ ካልሆነ ደግሞ የማሕበረሰብ ጤና ላይ መሥራት እንደምትችል አማራጮች ቀረቡላት።\n\n• ኤምአርአይ ምንድነው? \n\n• ከማህጸን ስለሚወጣ ፈሳሽ ምን ያህል ያውቃሉ?\n\n• የወንድሙን ገዳይ ለመበቀል ወደ ፈጠራ ሥራ የገባው ኢትዮጵያዊ \n\nያኔ ነው እናቶችና ሕፃናት ላይ ከስነ ተዋልዶ ጤና ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመሥራት የወሰነችው።\n\nሴቶች ላይ ለመሥራት ስትወስን ሃሳቡ ከባህር በላይ ሰፊ እንደሆነባት ታስታውሳለች፤ ስለዚህ ከሴቶች መብት ጋር በተያያዘ፣ የሴቶች ጥቃትን ለማስቆም የስነተዋልዶ ትምህርት ለመስጠት እንዲሁም የጡትና የማሕፀን ጫፍ ካንሰር ላይ ብትሠራ እንደምትወጣው ተረዳች። \n\nይህንን ፍንጭ ለማግኘት የረዳትን ስታብራራም በማሕበር ውስጥ 'ደብል ኢምፓክት' የተባለ ፕሮጀክት መኖሩ ነው ትላለች። ደብል ኢምፓክት በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንደማለት ነው። \n\nስለ ካንሰር ሲያስተምሩ የጡትና የማሕፀን ጫፍን በጋራ ማስተማር እንደማለት።\n\nበተለያዩ ተቋማት እየሄደች ስለጡትና ስለ ማህፀን ጫፍ ካንሰር ታስተምራለች፣ ጡታቸውን ራሳቸው እንዲፈትሹ፣ አልትራ ሳውንድና የማሞግራፊ ምርመራ እንዲያደርጉ መልዕክት ታስተላልፋለች።\n\nየማህፀን ጫፍ ካንሰርንም ቢሆን በአቅራቢያቸው በሚገኝ የጤና ጣቢያ ጎራ በማለት እንዲመረመሩ ታበረታታለች። በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን ለማስተማሪያነት አልያም ለመርጃ መሣሪያነት የሚያገለግል በኢትዮጵያ ቋንቋዎች የተዘጋጀ መርጃ ልታገኝ አልቻለችም።\n\nያኔ እቴጌ ተፀነሰች።\n\nእቴጌ ስትፀነስ ግን ከእርሷ ጋር አብረውት የሚማሩት፤ ሜሪ መሬሳ፣ መህቡባ በጊቾ፣ ቅድስት ዓለም ሰገድ አብረውኝ ነበሩ ትላለች።\n\nበአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ\n\nካንሰር ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች መካከል አንዱ ነው። በዓለማችን ላይ ካንሰር ብቻውን በየዓመቱ 7.9 ሚሊየን ሰው እንደሚገድል ጥናቶች ያሳያሉ። ምንም እንኳ እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ታዳጊ ሀገራት ውስጥ አሁንም በገዳይነት ግንባር ቀደምነቱን የያዙት ተላላፊ በሽታዎች ቢሆንም እንደ ካንሰር ያሉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችም እያደጉ ይገኛሉ።\n\nከሁሉም የካንሰር ዓይነቶች የጡት ካንሰር የከፋ መሆኑን የሚያሳየው እ.ኤ.አ. በ2018 የተደረገ ጥናት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተመዘገቡ የካንሰር ሕሙማን ቁጥር 25.5 በመቶው የጡት ካንሰር የተያዙ መሆናቸውን ያሳያል።\n\nበኢትዮጵያ ውስጥ የተደረገ አንድ ጥናት እንደሚያሳው በመላ ሀገሪቱ ከሚከሰቱ ሞቶች ካንሰር 5.8 በመቶውን ድርሻ ይይዛል። በኢትዮጵያ በካንሰር ታምመው ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች አብዛኛዎቹ በሽታው ከተሰራጨና ደረጃው ከፍ ካለ በኋላ እንደሚመጡ ቤተል ትናገራለች።\n\n• አመጋገባችን ማረጥን ሊያፋጥን ወይም ሊያዘገይ ይችላል\n\n• \"ዓላማችን ችግሮችን ፈተን ገንዘብ ማግኘት ነው \" የጠብታ አምቡላንስ ባለቤት\n\n• የሃምዛ ሃሚድ ገመድ አልባ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ \n\nበዓለማችን ላይ በስፋት ከሚታዩት የካንሰር ዓይነቶች መካከል...", "passage_id": "6dd6fadbe36e5deec311cb410b7f5112" }, { "passage": "\"አካል ጉዳተኝነት እንደፈተነኝ ይኖራል\"\n\n\"ዓይነ-ስዉር በመሆኔና ለእኔ የሚሆን ነገር በተወለድኩበት አከባቢ ባለመኖሩ እናቴ ትልቅ መስዋዕትነት ከፍላ ወደ ከተማ እንድመጣ አደረገችኝ\" በማለት የማይረሳዉን የህይወቷን ጉዞ ታስታዉሳለች።\n\nየ 35 ዓመቷ የትነበርሽ ንጉሴ፤ ዓይነ-ስዉርነቷ ገና በልጅነት እድሜዋ ነበር ከተወለደችበት ስፍራ ከ 800 ኪሎ ሜትሮች በላይ እንድትጓዝ ያደረጋት። \n\nበለጋ የዕድሜዋ ያጋጠማት የዓይን ህመም በተደረገላት ህክምና አልድን አለ። ይህንን ተከትሎ የትነበርሽ ሻሸመኔ ካቶሊክ ዓይነ-ስዉራን ትምህርት ቤት ትምህርቷን እንድትከታተል ተደረገ።\n\nዓይነ-ስውር መሆኗ ትምህርት እንድታገኝ ከማድረጉ በተጨማሪ በተወለደችበት አካባቢ ልማድ የነበረዉን ያለዕድሜ ጋብቻ እንድታመልጥ አድርጓታል። \n\nስለዚህም \"አካል ጉዳተኝነት ህይወቴን በሌላ አቅጣጫ እንዳይና ሌላ የህይወት ምዕራፍ እንዲኖርኝ አደርጓል\" ትላለች የትነበርሽ ንጉሴ።\n\nኅብረተሰብ እና ህግ\n\nኢትዮጵያ ካላት ህዝብ መካከል 17.5 በመቶ የሚሆኑት ወይም 15 ሚሊዮን ሰዎች አካል ጉዳተኞች እንደሆኑ የዓለም አቀፉ የሠራተኞች ድርጅት መረጃ ያመለክታል።\n\nይህ አሃዝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ካለው 15 በመቶ ጋር ሲነጻጸር በ 2.5 በመቶ ከፍ ያለ ነው።\n\n\"አካል ጉዳተኛ መሆኔ ጥሩ ደረጃ እንድደርስ አድርጎኛል\" የትነበርሽ ንጉሴ\n\nበኅብረተሰቡ ውስጥ ያለ የግንዛቤ እጥረት፣ የአካል ጉዳተኞች መብት ያለመከበር፣ አብዛኛዎቹ መሠረተ ልማቶች አካል ጉዳተኞችን ያገናዘቡ ያለመሆናችዉና ሌሎች መሰል ጉዳዮች ደግሞ በአገሪቱ ዉስጥ ያሉ የአካል ጉዳተኞችን ህይወት ፈታኝ የሚያደርጉ ናችዉ። \n\nየአካል ጉዳተኞችን ክብር የሚነኩና መስተካከል ያለባቸዉ ቃላት በተለያዩ ሀገር አቀፍ ሰነዶች ዉስጥ እንዳሉና መስተካከል እንዳለባችዉ የምትናገረዉ የትነበርሽ ንጉሴ የፍትሀ ብሄር ህግ አንቀጽ 339 እና 340'ን እንደምሳሌ ታነሳለች።\n\nበኅብረተሰቡ በኩልም ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች ቢኖሩም የሚታዩት የአመለካከት እና የግንዛቤ ችግሮች ቀላል እንዳልሆኑ ትናገራለች።\n\n\"አካል ጉዳተኝነት እንደፈተነኝ ይኖራል\"\n\nኢትዮጵያ ዉስጥ ሴት መሆን በራሱ ብዙ ፈተናዎች ያሉት ጉዳይ ነዉ ትላለች የትነበርሽ።\n\nየጾታ እኩልነት ግንዛቤ በደንብ ባልተስፋፋባት ሀገር ሴት አካል ጉዳተኛ መሆን ደግሞ ፈተናዉን ከባድ የሚያደርገው መሆኑን ትናገራለች።\n\n\"ይህ አመለካከት እየተሻሻለ መሆኑን መካድ ባልፈልግም፤ አሁንም ሴቶች እንደ ጠባቂ ነዉ የሚታዩት። አካል ጉዳተኛ ደግሞ እንደ እርዳታ ፈላጊ ነዉ የሚታየዉ። እነዚህ ሁለቱ ተደምረዉ የስኬታችን መንገድ ሩቅ እንዲሆን ያደርጋሉ።\"\n\n\"ሴትነት እና አካል ጉዳተኛነት የየራሳቸዉን ፈተና ይዘዉ ነዉ የሚመጡት\" የምትለዉ የትነበርሽ ንጉሴ፤ \"በሴቶች እኩልነት የሚያምን ህብረተሰብ ዉስጥ ብንሆን እንኳን አካል ጉዳተኛነት ራሱን የቻለ ፈተና ይሆንብናል\" ትላለች።\n\nለእናቷና ለአያቷ ትልቅ አክብሮት እንዳላት እና ለአሁኑ ስኬቷ ትልቅ ድርሻ እንዳላቸዉ የምታምነዉ የትነበርሽ፤ በሴትነቷ ብዙም ፈተና እንዳልገጠማት ገልጻ አካል ጉዳተኝነት ግን አሁንም እንደሚፈትናት ትናገራለች። \n\n\"ቀነኒሳ እና ኃይሌ ሲያሸንፉ ከንፈር አንመጥም። አካል ጉዳተኛ ሆነህ ስኬታማ ስትሆን ግን ከንፈር ይመጠጥልሃል። ነገር ግን ያሰዉ አካል ጉዳተኛ ከመሆኑ ባሻገር ብዙ የሚችለዉ ነገር ስላለ እንዳየነዉ ከንፈር ባንመጥ ጥሩ ነዉ\" ትላለች የዚህ ዓመት የአማራጭ ኖቤል ሽልማት አሸናፊዋ ሎሬት የትነበርሽ ንጉሴ። \n\nየግንዛቤ እጥረት የተለመደ ምክንያት\n\n\"አብረዉ ተጫዉተዉ ያደጉ ህጻናት ነገ አብሮ መስራት፣ መጋባት እንዲሁም አብረዉ ሃገር መለወጥ ይችላሉ\" የምትለዉ የትነበርሽ፤ ሌሎች ትምህርት... ", "passage_id": "0adc4aa1471ecad613b304ec2beed876" }, { "passage": "ሥራ ፈላጊን ሥራ ለማስቀጠር የሚከናወን ማንኛውም ተግባር፤  የቃል ወይም የጽሑፍ ማስታወቂያ፣ የምዝገባ፣ የምልመላና የምደባን ተግባራት የሚያጠቃልል ሁሉ ‹‹ሥራና ሠራተኛን ማገናኘት›› ተብሎ እንደሚጠራ አዋጅ ቁጥር 632/2001 በግልጽ አስቀምጧል፡፡ ሥራና ሠራተኛ አገናኝ  ድርጅቶች ፈላጊን ከተፈላጊ ጋር በማገናኘት ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡ በሠራተኛውና በአሠሪው ድርጅት በኩል የሚባክን ጊዜን በማስቀረት ምርታማነት እንዲጨምር ያደርጋሉ፡፡ ውጤታማነ ትንም በእጥፍ ያሳድጋሉ፡፡በኢትዮጵያ በኤጀንሲዎች በኩል ሥራና ሠራተኛን የማገናኘት አሠራር ከተጀመረ የቆየ ቢሆንም በርካታ የአሠራር ክፍተቶች እንደሚታዩ ይነገራል፡፡ ለእዚህ ወጣት ጠይባ ሀሰን አንድ ምስክር ነች፡፡ ኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ አካባቢ ነበር ያገኘናት፡፡ የመጣችው ከሰሜን ወሎ ሲሆን፤ ሳዑዲ አረቢያ በህጋዊ መንገድ ለሥራ የሚኬድበት ዕድል መመቻቸቱን ሰምታ ነው ወደ ስፍራው የመጣችው፡፡ለሥራ ወደ ውጭ ለመሄድ አዲስ አለመሆኗንና  የአሁኑ  ሦስተኛ ጊዜዋ መሆኑን አልደበቀችም፡፡ በሥራና ሠራተኛ አገናኞች በኩል የገጠማትን እንድትነግረን ጠየቅናት፤ ገንዘብ ተቀብሎ መጥፋት፣ ፓስፖርት መደበቅ፣ በተደጋጋሚ ውሸት መናገር፣ የሚነገረው የሥራ ዓይነትና የገንዘብ መጠን የተለያየ መሆን ከገጠሟት ችግሮች ጥቂቶቹ ናቸው።ወጣት እንድሪስ ጸጋዬ ከወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በጂኦሎጂ የትምህርት ዘርፍ ክፍል 3 ነጥብ ሥድስት አራት አስመዝግቦ 2008 ዓ.ም ተመርቋል፡፡ ሁለት ዓመታትን ያለ ሥራ አሳልፏል፡፡ ያገኘነው በለገሃር አካባቢ የሥራ ማስታወቂያ ሲያነብ ነበር፡፡ ሥራ ለመያዝ ያልደወልኩለት ኤጀንሲ የለም ይላል ወጣት ጀማል፡፡ በየቦታው ሥራ እናስቀጥራችኋለን የሚሉ ሌቦች እንደ አሸን ፈልተዋል፡፡ሕጋዊ ይሁኑ ሕገ ወጥ መለየት አይቻልም፡፡ የትምህርት ማስረጃህን ኮፒ ሲቀበሉህ ጀምሮ ሥራ ተገኝቶልሃል በሚል እየጠሩ ገንዘብ እንድትከፍል ይጠይቁሃል ሲል ይገልጻል፡፡በአዲስ አበባ ከተማ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሥራ ሥምሪት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ካሣ ሥዩም እንደገለጹት፤ በሥራና ሠራተኛ ማገናኘት አገልግሎት ዘርፍ የሚስተዋሉት ችግሮች አያሌ ናቸው፡፡ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ሥራና ሠራተኛ አገናኞች በችግር የተተበተቡ ናቸው፡፡ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥ የሆኑ ጥያቄዎች ከሕብረተሰቡ፣ ከመገናኛ ብዙሃን አካላት፣ ከተቀጣ ሪው ሠራተኛና ከኤጀንሲዎች ጭምር ይነሳሉ ብለዋል፡፡ሠራተኛና ማህበራዊ ቢሮ ባደረገው ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የዳሰሳ ጥናት መሰረት ችግሮቹ በሁለት ይመደባሉ፡፡ የመጀመሪያው በአገልግሎት አሰጣጡና በሥራ ሥምሪት ዙሪያ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ኤጀንሲዎች ከሦስተኛ ወገን ሥራን ተረክበው ሠራተኛ ራሣቸው ቀጣሪ ሆነው በሚሠሩበት ወቅት ከአሠሪና ሠራተኛ መብትና ግዴታ የሚመነጩ ችግሮች መሆናቸውን ተለይቷል፡፡ ለእነዚህ ችግሮች መፍትሔ ለመፈለግ የአገሪቱ የአሠሪና ሠራተኛ ሕጎች ምን እንደሚመስሉ መፈተሽ ተገቢ መሆኑን ዳይሬክተሩ አቶ ካሣ አንስተዋል፡፡የመጨረሻው መረጃና ጥናት ላይ ያተኮረ ነው፡፡ በመሆኑም የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ መረጃ መሰብሰብ፣ ጥናቶችን ማካሄድ፣  ትንበያዎችን ማድረግና መረጃ ማሰራጨት ላይ የሚያተኩር መሆኑ በመመሪያው ተመላክቷል፡፡ ይህ የተጠቀሰው ለአብነት ያህል እንጂ አገራችን ያፀደቀቻቸው ወይም የምታፀድቃቸው ኮንቬንሽኖች የአገሪቱ የሕግ አካል እንደሆኑ/እንደሚሆኑ ሕገ-መንግሥቱ ሕጋዊ መሠረት አስቀምጧል።በዚህ መሰረት በኢትዮጵያ በዓለም ሥራ ድርጅት የወጡ 21 ስምምነቶች ፀድቀው የአገሪቱ የሕግ አካል ሆነው ሥራ ላይ እንዲውሉ ተደርጓል ያሉት ዳይሬክተሩ አቶ ካሣ ሥዩም ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች በዚች አገር ላይ እንዲኖሩ ከሚያደርጉ ምክንያቶች አንዱ ከእነዚህ ሥምምነቶች የሚመነጭ መሆኑን ተናግረዋል፡፡በአዋጅ ቁጥር 632/2001 እንደተመለከተው፤ የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ  መንግሥታዊ አካል ያልሆነ፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከሠራተኛው ገንዘብ ሳይቀበል የሥራ ውል ተዋዋይ ወገን ባለመሆን በአገር ውስጥ ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘት ወይም ከሠራተኛው ጋር የሥራ ውል ስምምነት በማድረግ ሠራተኛን በአገር ውስጥ ወይም በውጭ አገር ለሥራ ለሦስተኛ ሰው የማቅረብ ወይም ሁለቱንም አገልግሎቶች አጣምሮ የሚሰጥ የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው በማለት አስቀምጧል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ መብራቴ በበኩላቸው በከተማዋ ባለፉት ሁለት ዓመታት የኤጀንሲ ፈቃድ አውጥተው በአገልግሎቱ ዘርፍ የተሰማሩት 454 ተቋማት መሆናቸውን ያብራራሉ፡፡ በተደረገ ክትትልም ከተፈቀደላቸው ሕጋዊ ተግባርና ኃላፊነት ውጪ የተለያዩ ጥፋቶች መፈጸማቸውን በማረጋገጥ የእርምት ዕርምጃ ተወስዷል፡፡ በመሆኑም 128 ኤጀንሲዎች ፈቃዳቸው ተሰርዟል፡፡ 23 ኤጀንሲዎች ፈቃድ መልሰዋል፡፡303 ኤጀንሲዎች  አሁን በሥራ ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል 116 ኤጀንሲዎች ፈቃዳቸው የሥራ ውል በማዋዋል ሲሆን፤ 187 በማገናኘት ብቻ ፈቃድ ያወጡ ናቸው፡፡ በሕጋዊ ሽፋን ሕገ ወጥ ተግባር የሚሠሩ አሉ የሚሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ በ222 ኤጀንሲዎች ላይ ክትትል ተደርጓል፡፡ በመሆኑም 81 ኤጀንሲዎች ፈቃድ ባወጡበት የመስሪያ ቦታ አለመገኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ሥራና ሠራተኛ በማገናኘት ብቻ የተሰማሩ 28 ኤጀንሲዎች በሕገ ወጥነት በርካታ ገንዘብ ከሥራ ፈላጊዎች ሰብስበው የተገኙ መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ ከድግሪ ምሩቃን ሥራ ፈላጊዎች ከአራት ሺህ ብር እስከ ሥምንት ሺህ ብር በሰው ሲያስከፍሉ እንደነበረ ማስረጃዎች መገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡አቶ ካሣ ሥዩም የሥራ ውል ተዋዋይ ወገን በመሆን ለሦስተኛ ወገን ሥራ የሚያሠሩ ሕጋዊ ፈቃድ ያወጡ 116 ኤጀንሲዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ ይሁን እንጂ ሕግና መመሪያን ተከትሎ የመሥራት ችግር ያለባቸው መሆኑን በክትትልና ቁጥጥር ከታች የተዘረዘሩት ችግሮች መለየታቸውን ገልጸዋል፡፡ሠራተኞች የሥራ ላይ አደጋ ሲደረስባቸው የህክምና ወጪ አለመሸፈን ፣ በህዝብ በዓላት ቀን  በሥራ ላይ ለሚሰማሩ ሠራተኞች በህጉ መሠረት ክፍያ አስልቶ አለመፈፀም፣ በማህበር የመደራጀት መብት አስቸጋሪና ፈታኝ መሆኑ፣ የደመወዝ ጭማሪ፣ ቦነስና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን ሠራተኞች እንዲያገኙ ለማድረግ ትኩረት ያለመስጠት፤የሥራ አልባሳትና መጫሚያዎች በወቅቱ ያለመስጠት፤ሥራ ሲለቁ የተሰጠ የግል አልባስትና መጫሚያዎች ካልመለሳችሁ የሥራ ልምድና መልቀቂያ አንሰጥም በማለት በመያዥነት የመያዝ፤ በአንዳንድ የሥራ ዘርፎች በኤጀንሲ ተቀጥረው በሥራ ላይ የተሰማሩ ሠራተኞች ከአንድ በላይ ለሆኑ አሠሪዎች ክትትልና ቁጥጥር የተዳረጉ ሆነውም ተገኝተዋል፡፡ምክትል ቢሮ ኃላፊው አቶ አሰፋ መብራቴ በበኩላቸው፤ ኤጀንሲዎች ከነችግራቸውም ቢሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት 54‚624 (ወንድ 34‚548 እና ሴት 20‚076) ሥራ ፈላጊዎችን ለሥራ ማብቃታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ 995 ሕገወጥ ኤጀንሲዎች ሥራ ፈላጊውን ማህበረሰብ በማታለል መሰማራታቸው በክትትል ተደርሶበታል፡፡ ሕጋዊ ዕርምጃም ተወስዷል፤በመወሰድ ላይም ይገኛል ብለዋል፡፡አዲሰ ዘመን ጥር 2/2011መሀመድ ሁሴን  ", "passage_id": "c72404bfb82d7634ec810231aa8a3389" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም (አብመድ) ለዘመናት በተሰራው የተሳሳተ ትርክት ብሔርን መሰረት ያደረገው ጥቃት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በደቡብ እና በኦሮሚያ ክልሎች በሚኖሩ አማራዎች ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመባቸው ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ የህግ ማብራሪያ እንዲሰጡን ከአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የህግ ጉዳዮች አማካሪ መርኃጽድቅ መኮንን ጋር አብመድ ቆይታ አድርጓል።እንደ አቶ መርኃጽድቅ ማብራሪያ በቀደሙት ዘመናት የአማርኛ ተናጋሪው ሌላውን ማኅበረሰብ ተጭኖ እንደኖረ ተደርጎ በተሰበከው ጥላቻ ፅንፈኛ አካላት በተደራጀ መንገድ ብሔር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እያደረሱ ነው፡፡ የለውጥ ማሻሻያ እርምጃዎች ከተወሰዱ በኋላ አማራውን ዒላማ ያደረገ ጭፍጨፋ መድረሱን የተናገሩት የህግ ጉዳዮች አማካሪው “ይህንን በድፍረት ለመናገር በመንግሥት አካላት ላይም ድፍረቱም የለንም፤ ከፍተኛ የሆነ የወንጀል ጥቃት እየደረሰ ነው፤ የተደራጀ ወንጀል እየተፈጸመ ነው፤ ድርጊቱን በስሙ የመጥራት ድፍረት ሊኖረን ይገባል” ብለዋል።በቀደሙት ዘመናት ህወሀት እና ኦነግ አማራው ከስልጣን ገለል እንዲል፣ በኢኮኖሚ እንዲዳከም በሌላው ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ የጥላቻ ስብከት ለዘመናት ሲሰሩ መቆየታቸውን የህግ አማካሪው አስረድተዋል። የተከማቸው ጥላቻ ሙሉ በሙሉ እንዲወገድ የማይፈልጉ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ አሁንም ያሉ አካላት እንዳሉ ጠቁመዋል፡፡ የመንግሥት መዋቅሩ ከቀበሌ እስከ ፌዴራል ያልተቀየረ በመሆኑ በአማራው ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ማስቆምና በዘላቂነት ለመፍታት ውስብስብ እንዳደረገው ተናግረዋል። “የህግ አስከባሪ አካላት ራሳቸው ምን ያህል ከችግር የፀዱ ናቸው የሚለው ጉዳይም አነጋጋሪ ነው” ብለዋል አቶ መርኃፅድቅ፡፡አማካሪው በማብራሪያቸው መንግሥት በዚህ አካሄድ ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ የህግ የበላይነትን እያስከበረ ነው ለማለት እንደማያስደፍር ጠቅሰዋል፡፡ አማካሪው መርኃጽድቅ መኮንን የመንግሥት ቀዳሚ ተግባር የኅብረተሰቡን ሠላም እና ደኅንነት ማስጠበቅ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ ዜጎች በየአካባቢው ያለውን የህግ የበላይነት ተማምነው በሠላማዊ መንገድ ሥራቸውን አከናውነው እንዲገቡ መንግሥት ቁልፍ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።መንግስት ይህንን ኃላፊነት መወጣት ካልቻለ በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ዘንድ ተቀባይነትን እና ተአማኒነትን እንደሚያሳጣው ያብራሩት የሕግ አማካሪው መርኃጽድቅ የኢትዮጵያ ህገ መንግስት አንቀጽ 28 በስብእና ላይ ስለሚፈጸሙ ወንጀሎች አሁን እየሆነ ያለውን ብሔር ተኮር ጥቃት በከፍተኛ ወንጀል ደረጃ የሚፈርጅ እንደሆነም ተናግረዋል። አሁን እየተፈጸመ ያለውን ብሔር ተኮር ጥቃት የሀገሪቱን ህገ መንግስት እና የዓለም አቀፍ ህጎችን የጣሰ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲሉም አስረድተዋል። ብሔርን መሰረት ተደርጎ እየደረሰ ያለው የዘር ማጥፋት ድርጊት ደግሞ በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ ሕጎች ይቅርታ እና ምህረት እንኳን የማያሰጥ ወንጀል እንደሆነ ማብራሪያ ሰጠዋል።በተለይም ዜጎችን በማንነት፣ በብሔር፣ በሚናገሩት ቋንቋ እና ባህላቸውን አነጣጥሮ የጅምላ ወንጀል መፈጸም በሀገሪቱ የወንጀል መቅጫ ህግም ከ25 ዓመታት እስከ ፅኑ እስራት የሚያስቀጣ ለአብነት ጠቅሰዋል። አቶ መርኃጽድቅ መኮንን በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀጽ ዘጠኝ ንዑስ አንቀጽ አራት ሥር እንደተደነገገው ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሕጎችን የራሷ የሕግ አካል አድርጋ ስለተቀበለች አጥፊዎችን በዚህ ሕግ ልትጠይቅ እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ለመከላከል እና ለመፍታት በ1948 ዓ.ም በታኅሣሥ ወር ላይ የተደነገገው እና በተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባዔ ቁጥር 260/A3 የጸደቀውን ሕግን ተስማምታ መፈረሟንም ነግረውናል፡፡የሕግ ምሁሩ በዚህ ስምምነት አንቀጽ 2 ሥር ደግሞ መግደል፣ ዘር ማጥፋት፣ ማደን፣ ማሳቀቅ፣ ዘር እንዲጠፋ ቅድመ ሁኔታዎችን ማስቀመጥ በዝርዝር እንደተደነገጉ አስረድተዋል። ድርጊቱን ማንም ይፈፅም ማን ኃላፊነቱን የሚወስደው በዚያ አካባቢ የሚገኘው የመንግስት አካል እንደሆነም አቶ መርኃጽድቅ መኮንን አስገንዝበዋል። በአካባቢው የሚገኝ የፀጥታ አካል፣ ደኅንነት፣ የመከላከያ ሰራዊት እና ወታደራዊ ሃይል እነዚህን ጥቃቶች መከላከል ካልቻለ የመንግሥትን እና የዜጎችን ህልውና መታደግ እንደማይችልም ለአብነት ጠቅሰዋል። አደገኝነቱ ለሕዝብ ብቻ ሳይሆን ለመንግሥትም ጭምር መሆኑን በመጥቀስ። እናም በተደራጀ መንገድ መከላከል አስፈላጊ እንደሆነ አሳስበዋል፡፡አቶ መርኃጽድቅ መኮንን እንዳሉት ሕዝቡ ለዘመናት አብሮ የሚኖር እና የማይነጣጠል በመሆኑ ጥቃት አድራሾችን በጋራ ሊከላከላቸው ይገባል፤ ጥቃት የሚደርስባቸው ዜጎች ቁጥር እየበዛ በመሆኑ የችግሩን ክብደት ማመን እና ሙሉ አቅምን በመጠቀም መቋጫ መፍትሔ መፈለግ እንደሚገባ የህግ አማካሪው ተናግረዋል። በተለይም በብሔር ፌዴራሊዝም ላይ የተመሰረተን ሕገ መንግሥት ጽንፈኞች ላልተገባ ጥቅም ሲያውሉት እየታየ በመሆኑ ሕገ መንግሥቱ እሰኪ ለወጥ ድረስ የክልል እና የፌዴራል መንግሥታት የዜጎችን ደኅንነት መጠበቅ እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ መንግስት ደግሞ ያለምንም አድሎ ሁሉንም ዜጎች የመጠበቅ ግዴታ እንዳለበት በህገ መንግስት አንቀጽ 25 እና 32 ስለሚደነግግ ይህንን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡", "passage_id": "93221528e1b9cfaef224f14a76f9a340" } ]
2ed56a19309c9dddae2f7bac04989cb2
53b0a418ce57380fec0b2127aadfb596
ኤጀንሲው ከኦፓል የወጪ ንግድ 210 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት፤ ለ604ሺ በላይ ዜጎችም የሥራ ዕድል ለመፍጠር አቅዷል
 ኤጀንሲው ከኦፓል የወጪ ንግድ 210 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት፤ ለ604ሺ በላይ ዜጎችም የሥራ ዕድል ለመፍጠር አቅዷል  አስናቀ ፀጋዬአዲስ አበባ፡- ከኦፓል ማዕድን የወጪ ንግድ 210 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት በአስር ዓመቱ መሪ እቅድ ውስጥ አካቶ እየሰራ እንደሚገኝ የአማራ ክልል ማዕድን ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ገለፀ። በዚሁ ዘርፍም ለ604 ሺ 210 ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ማቀዱን ተናግሯል።፡የአማራ ክልል ማዕድን ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ይታየው ተስፋሁን ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ ኤጀንሲው ከኦፓል ማዕድን የወጪ ንግድ በአስር ዓመቱ መሪ አቅድ ውስጥ 210 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት አቅዷል። ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንፃርም በኦፓል ማዕድን ማምረት ሥራ ለ604 ሺ 210 ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር አስቧል።እንደ ኃላፊው ገለፃ፤ ከውጪ ምንዛሬ ገቢ በተጨማሪ በዚሁ የአስር ዓመት መሪ እቅድ ውስጥ ኤጀሲው ከሮያሊቲና ከአገልግሎት ክፍያ 1 ቢሊዮን 117 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ወጥኗል። ይህንኑ እቅድ ለማሳካትም በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ለሚገኙ የዘርፉ ፈፃሚዎች ስልጠናዎች እየተሰጡ እንደሚገኙና በቀጣይም ስልጠናው ለሌሎች በተከታታይ የሚሰጥ ይሆናል። በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ኤጀንሲው ሃያ የሚሆኑ የምርመራና የማምረት ፍቃድ ለአልሚዎች መስጠቱንም የጠቀሱት ኃላፊው፤ ኅብረተሰቡና ባለሀብቱም ጥቅሙን በመረዳት ወደዚህ የማዕድን ማምረት ሥራ እየተሳበ እንደሚገኝም አመልክተዋል። ይህም በቀጣይ ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል። በ2013 ዓ.ም ብቻ ባጠቃላይ 44 ሺ 125 ለሚሆኑ ዜጎች በማዕድን ዘርፍ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ኤጀንሲው እቅድ መያዙንም አያይዘው የገለፁት ኃላፊው፤ ከውጭ ምንዛሬ አኳያ 18 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘትና ከሮያሊቲና አገልግሎት ክፍያም 100 ሚሊዮን ብር የሀገር ውስጥ ገቢ ለመሰብሰብ ማሰቡን ጠቁመዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38345
[ { "passage": "ዘንድሮ ከማኑፋክቸሪንግ ምርቶች ዘርፍ ከ913 ነጥብ 6 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር በላይ ለማግኘት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የንግድ ሚኒስቴር አስታወቀ ፡፡የሚኒስቴሩ የውጪ ንግድ ማስፋፊያ ዳሬክቶሬት ጀነራል ዳይሬክተር አቶ አሰፋ ሙሉጌታ ለዋልታ እንደገለጹት፤የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማስፋት ወደ ውጭ ከሚላከው ምርት የሚገኘው ገቢ  በሶስት እጥፍ ለማሳደግ እየሰሩ ይገኛሉ ፡፡ማንፈከቸሪንግ ምርቶቹ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ጨርቃጨርቅና አልባሳት ፣ምግብ መጠጥና ፋርማሲቲካል ፣ኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብአቶች፣ ስጋና ወተት ተዋጽኦዎች ፣ብረታብረት ፣ስኳርና ሞላሰስ መሆናቸውን ጠቁመዋል ፡፡ከነዚህም ውስጥ ቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ ጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ምግብ መጠጥና ፋርማሲቲካል፣ ስጋና ወተት ተዋጽኦዎች እሴት የሚጨመርባቸው ናቸው ብለዋል፡፡ስለሆነም የተሻለ ገቢ ለማግኘት ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ጥራትን ማሻሻል ተሳቢ መደረጉን ገልጸዋል ፡፡እንደዚሁም ዘመናዊ የግብይት ስርዓትን ማስፋት እና የተሳለጠ በማድረግ በሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በአሰራር እየተመለሱ እንደሚሄዱ አብራርተዋል ፡፡በተለይም የኢንዳስትሪው ፓርኮቹን እንደ አንድ ግብኣት በመጠቀም በተሻለ በደገፍና በጠናከር መስራት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል ፡፡በተለይም ህገ ወጥ ንግዱን በተለየ መልኩ የመከላከልና አቅርቦቱን ማሻሻል ላይ ስራ ይካሄዳል ብለዋል ፡፡ዘርፉን ቀልጣፋ ለማድረግ የሎጂስቲከስ የጉሙሩክ አሰራሮችን የበለጠ በመቃኘት በቅንጅት መስራት መሆኑን አስታውቀዋል ፡፡በለፈው ዓመት ከማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ከ300 ሚሊየን ዶላር በላይ መገኘቱን ለማወቅ ተችሏል ፡፡", "passage_id": "2221c88a779276f5d05c691704b405ff" }, { "passage": "በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ማብቂያ፣ ከማዕድን ወጪ ንግድ በየዓመቱ ሦስት ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ለመሰብሰብ ታቅዷል፡፡የማዕድን ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዙሪያ ከመስከረም 20 እስከ 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በሚኒስቴሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ውይይቱን የሚመሩት የማዕድን ሚኒስትሩ አቶ ቶሎሳ ሻጊ ለሪፖርተር እንደገጹት፣ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን መጠናቀቂያ ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በየዓመቱ ከማዕድናትና ከጋዝ ወጪ ንግድ ሦስት ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዷል፡፡ የውጭ ምንዛሪውን በዋነኛነት ለማግኘት የታቀደው ከወርቅ፣ ከፖታሽ፣ ከታንታለምና ከተፈጥሮ ጋዝ ኤክስፖርት እንደሆነ አቶ ቶሎሳ አስረድተዋል፡፡በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ኦጋዴን ክልል ውስጥ የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ለማልማት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ የገለጹት አቶ ቶሎሳ፣ በ2010 ዓ.ም. ወደ ምርት ይገባል ተብሎ እንደሚታሰብ ተናግረዋል፡፡ በተመሳሳይ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን በአፋር ክልል ውስጥ ዳሎል አካባቢ የሚገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው የፖታሽ ማዕድን ለማልማት ጥናት ሲያካሂዱ የቆዩት ያራና ሰርኪውም ሪሶርስ የተሰኙ ኩባንያዎች ወደ ምርት ይሸጋገራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡አላና ፖታሽ የተሰኘው የካናዳ ኩባንያ በፖታሽ ምርት ለመሰማራት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ሰፊ የፍለጋና የምርመራ ጥናት ካካሄደ በኋላ ከማዕድን ሚኒስቴር ጋር የከፍተኛ የማዕድን ምርት ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ ኩባንያው እንደታሰበው ወደ ምርት ሳይገባ ቀርቷል፡፡ ‹‹አላና ፖታሽ በዓለም ገበያ ከፖታሽ ዋጋ ማሽቆልቆል ጋር ተያይዞ እንዳሰብነው አልሄደልንም፤›› ብለዋል አቶ ቶሎሳ፡፡ አላና የፖታሽ ይዞታውን አሳልፎ እስራኤል ኬሚካልስ ለተሰኘ ግዙፍ የእስራኤል ኩባንያ የሸጠ ቢሆንም፣ ማዕድን ሚኒስቴር የሽያጭ ውሉ በአግባቡ እንዳልተገለጸለት አስታውቋል፡፡ ‹‹እኛ የሰማነው ወሬውን ነው እንጂ ፎርማል በሆነ መንገድ አልተገለጸልንም፡፡ ስለዚህ እኛ የምናውቀው አሁንም አላና መኖሩን ነው፤›› ብለዋል አቶ ቶሎሳ፡፡በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን የወርቅ ምርት በከፍተኛ መጠን እንደሚጨምር ይጠበቃል፡፡ አዳዲስ የወርቅ ማውጫ ያቋቁማሉ ተብለው የሚጠበቁት ከፊ ሚኒራልስ (ወለጋ ውስጥ) ሚድሮክ ጎልድ (መተከል)፣ አስኮም ማይኒንግ (ቤኒሻንጉል) እና ኢዛና ማይኒንግ (ትግራይ) ውስጥ ናቸው፡፡ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከማዕድን ኤክስፖርት 500 ሚሊዮን ዶላር ታገኛለች፡፡ ከዚህ ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዘው የወርቅ ኤክስፖርት ነው፡፡ በዓለም አቀፍ ገበያ የወርቅ ዋጋ በማሽቆልቆሉ በ2006 ዓ.ም. ጀምሮ ከማዕድን ኤክስፖርት የሚገኘው የውጭ ምንዛሪ ቀንሷል፡፡ ይህንን ለማካካስ የማዕድን ሚኒስቴር የተለያዩ ሥራዎች በመሥራት ላይ እንደሚገኝ አቶ ቶሎሳ ተናግረዋል፡፡ የከበሩ ድንጋዮችና ጌጣ ጌጥ ኤክስፖርት መጨመር፣ የታንታለም ምርት መጨመርና የፖታሽ ምርት መጀመር ተጠቃሽ ናቸው፡፡በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ በተካሄደው ውይይት የማዕድን ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ዓለሙ ስሜ፣ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ለኢንዱስትሪ ማዕድናት ትኩረት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ዓለሙ የማዕድኑ ዘርፍ ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኮንስትራክሽንና ለግብርና ዘርፎች ግብዓት በማምረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡", "passage_id": "0470b75b75b08fa0fb973711fc072ef7" }, { "passage": "ለምለም መንግሥቱ አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ በ2022ዓ.ም ሰባት ነጥብ ሦስት ሚሊዮን የሚሆን ቱሪስት በመሳብ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ 23 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ እየሰራች መሆኑ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ተናገረ። በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የቱሪዝም ዘርፍ አማካሪ አቶ አህመድ መሐመድ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በአስር ዓመቱ መሪ ዕቅድ የመጨረሻ ዓመት በሆነው 2022 ዓ.ም ሰባት ነጥብ ሦስት ሚሊዮን የሚሆን ቱሪስት በመሳብ 23 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ ለማግኘት እየተሰራ ነው። በዚህም አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዷል። አቶ አህመድ እንደሚሉት፤ በሀገር ደረጃ አዲስ የሆነውን የቱሪዝም ኤክስፖርት በመተግበርና 26 በመቶ ድርሻ እንዲኖረው በማድረግ ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ በማድረስ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ወደ ትግበራ የተገባ ሲሆን፤ መሪ ዕቅዱም ለቱሪዝም ዕድገት ማነቆ የነበሩ ችግሮችን በመለየት ዘርፉን በሚያሳድጉት ላይ ቢሰራ የሚፈለግበት ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚቻል የሚያሳይ ነው። ይህ እንዲሆን ደግሞ ተወዳዳሪነትን መፍጠር፣ የመረጃ ልዕቀትን ማጎልበት፣ ጥናትና ምርምር ማካሄድ ላይ ትኩረት ማድረጉን የጠቆሙት አቶ አህመድ፤ በሀገሪቷ እየተገነባ ካለው ዕውቀት መር የኢኮኖሚ ሥርዓት ጋር ቱሪዝምን ለማስተሳሰር ጥራት ያለው ጥናትና ምርምር እንዲሁም ዕውቀት በማጎልበት ላይ ሥራዎች እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በትኩረት ከተሰራም ቱሪዝምን ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ ይቻላል የሚል እምነት መያዙን አስረድተዋል። በዓለም የቱሪዝም ገበያ ውስጥ እነ ቻይና፣ ጃፓን፣ ሩሲያ እና የመካከለኛ ምሥራቅ ሀገራት እየገቡ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ አህመድ፤ እነዚህን ማዕከል ባደረገ የቱሪዝም መዳረሻና አቅርቦት መኖር አለበት በሚል ዕቅዱ መቃኘቱንም አመልክተዋል። ተመልካች ብቻ ሳይሆን በሚጎበኘው አካባቢም ተሳትፎ ያለው ቱሪስት ነው የሚፈለገው ብለዋል። ቱሪዝም አካታች የቱሪዝም ገበያ ነው ያሉት አቶ አህመድ፤ ለሕግ የሚገዛ፣ በእውቀት የሚመራ፣ በቀጣሪና በተቀጣሪ መካከል መልካም ግንኙነት እንዲሰፍን የሚያደርግ ሥርዓት በመፍጠር የጎላ ሚና እንዲኖረው፣ በአነሥተኛ፣ በመካከለኛና በከፍተኛ የተደራጁ አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ዘርፉን እንዲቀላቀሉ፣ ሆቴል ቤቶችም እንዲስፋፉ እስትራቴጂው የሚያግዝ እንደሆነ አስረድተዋል። ዕቅዱ በተዘጋጀበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ ተገዳ ወደ አላስፈላጊ ጦርነት እንድትገባ ያደረጋት ነገር አዲስ ክስተት ነው ያሉት አቶ አህመድ፤ በአሁኑ ጊዜ ወደተረጋጋ ሥርዓት እየገባች በመሆኑ ዘርፉ መልሶ እንዲያንሰራራ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙኃንን ሳይቀር በመጠቀም የማስተዋወቅ ሥራው ይጠናከራል ብለዋል። በመንግሥት ሕግን ለማስከበር የወሰደው እርምጃ ዓለምአቀፍ ተቀባይነትን ለመጨመር እንደ አንድ የፖለቲካ አቅም መወሰዱን አቶ አህመድ ጠቁመው፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙኃንን ሳይቀር በመጠቀም ያደረገው እንቅስቃሴ በቱሪዝም ዘርፉ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችል ነበር ብለዋል። ነገር ግን ፖለቲካል ካፒታል የሚባለው የዲፕሎማሲ እና ሌሎችም ጥረቶች ግጭቱን በፍጥነት ለመቀልበስ እንዳስቻላትም አንስተዋል። የአስር ዓመቱ የቱሪዝም\nመሪ ዕቅድ ላይ\nበዘርፉ በቀጥታና በተዘዋዋሪ\nተሳታፊ የሆኑ አካላት፣\nበከፍተኛ አመራር ላይ\nያሉ የተቋሙ ሠራተኞች፣\nበዘርፉ ላይ ከፍተኛ\nእውቀት ያላቸው የተካተቱበት\nአካላት ያዘጋጁትና ተተችቶ\nየዳበረ ሰነድና ለትግበራ\nየበቃ እንደሆነ አቶ\nአህመድ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2013", "passage_id": "7894b015fbd1563e1b6be55c927393a5" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ እስከ አሁን ከ 38 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማስገኘቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ። ለ23 ሺ ዜጎችም የሥራ ዕድል መፍጠሩንም ገልጿል።የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ መኮንን ኃይሉ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳሉት፤ በፓርኩ ውስጥ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ዘርፍ የተሰማሩ 19 የውጭ እና አንድ የአገር ውስጥ ኩባንያዎች ገብተው እየሠሩ ይገኛሉ።ኩባንያዎቹ ምርቶቻቸውን በዋነኝነት ወደ አውሮፓና አሜሪካ ገበያ እየላኩ መሆናቸውን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፣ ኢትዮጵያ በአገዋ የገበያ ዕድል  በመጠቀም ወደ አሜሪካ ገበያዎች ለመግባት ሰፊ ዕድል እንደተፈጠረላት ገልጸዋል፡፡ በአውሮፓ ገበያም እንዲሁ እንደ አገዋ ያለ ኢ.ቤ.ኤ የተሰኘ  ድርጅት አባልም መሆኗን ጠቅሰው፣በዚህም ምርቶቿን ከቀረጥ ነጻ ወደ አውሮፓ ገበያ እያስገባች እንደምትገኝ አመልክተዋል። እነዚህንና ሌሎች መሰል የገበያ አማራጮችን መጠቀሟ የምታገኘው  ገቢ ከፍ እንዲል እንደሚረዳም አቶ መኮንን አስታውቀዋል፡፡በፓርኩ  የባንክ፣ የኤሌክትሪክ፣ የቴሌኮም፣ ኢሚግሬሽን ፣  የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ  አገልግሎቶች እንዲሁም የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ፣ የኢትዮጵያ ጨርቃጨርቅ ኢንስቲትዩትን ጨምሮ ሌሎችም የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ለኩባንያዎቹ  እየተሰጡ መሆናቸውን  ጠቁመዋል።‹‹ፓርኩ ከሌሎች የሚለይባቸው በርካታ ነገሮች አሉ›› ያሉት አቶ መኮንን፣ አንዱ ከሚሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ ሥራ አስኪያጆች እንዲሁም የዘርፉ ኤክስፐርቶች አቅማቸውን ለመገንባት የሚያስችላቸው የሥልጠና ማዕከል የሚገኝበት መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ብቸኛው የማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ ባለቤት  እንዲሁም  የፓርኩን ተረፈ ምርቶች እንደገና በመፍጨት በፓርኩ ያሉ ኩባንያዎች ለተለያዩ አገልግሎቶች እንዲጠቀሙበት የሚያደርግ መሆኑን ሌሎች ልዩ የሚያደርጉት መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ቀደም ብለው ወደ ሥራ ከገቡት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ወቅትም ለ23 ሺ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል።በቀጣይም የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመረቆ ወደ ሥራ ይገባል ተብሎ እየተጠበቀም ይገኛል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2011በእፀገነት አክሊሉ", "passage_id": "17ae8323c439651487989728d20a802e" }, { "passage": "ከዓለም ባንክ በተገኘ 5.5 ቢሊዮን ብር ድጋፍ በአገር አቀፍ ደረጃ በአነስተኛና በመካከለኛ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር በዝግጅት ላይ መሆኑን፣ የፌዴራል አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ይህንን ያለው ታኅሳስ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡ በወቅቱም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓት አቅራቢ ድርጅቶች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔዎችና ሌሎች ተቋማት በተገኙበት መሆኑ ተገልጿል፡፡ የፌዴራል አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ማስፋፊያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስፋው አበበ እንደተናገሩት፣ በአገሪቱ 20 ሺሕ የሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ አምራቾች ይገኛሉ፡፡ እነዚህን አምራቾች ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ ዘላቂ የሆነ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የሚሠራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥረው ይህ ፕሮጀክት፣ ከዚህ በፊት የተጀመሩና የተስተጓጎሉ ነገሮች ተስተካክለው፣ በተሳካ ሁኔታ የሚቀጥሉበት መንገድ የሚያመቻች መሆኑን አክለዋል፡፡ ከዚህ በፊት ይደረግ የነበረው ድጋፍ ጥናት ላይ ያልተመሠረተና ቅንጅታዊ አሠራር ያልታየበት በመሆኑ፣ ከዘርፉ ሊገኝ የሚገባውን ውጤት ማግኘት አለመቻሉን አቶ አስፋው ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የተገኘውን የገንዘብ ድጋፍ በመጠቀም ትክክለኛ ፍላጎታቸውን አቅርበው ወደ ሥራ ዘርፉ ውስጥ መግባት የሚችሉበት መንገድ የተመቻቸ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በአገሪቷ ከፍተኛ የሆነ የሥራ አጥ ችግር በመኖሩ የሚፈለገውን ያህል ዘላቂ የሆነ የሥራ ዕድል መፍጠር የሚቻለው የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ በመሥራት፣ እንዲሁም የፋይናንስ፣ የግብዓት፣ የማምረቻ ቦታ ይዞታ ለሥራ አጦች በማሟላት ጭምር ነው ሲሉ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ሥራ አጥነትን ለመቀነስና ኢኮኖሚውን ለማንቀሳቀስ በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ላይ መሠረት መጣል እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል፡፡ ለአነስተኛና መካከለኛ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ተብለው የሚቀርቡ የመሥሪያ ቦታ፣ የግብዓትና የብድር አቅርቦት ለሌላ ዓላማ የሚያውሉ ተቋማትን በመለየት በዘርፉ ላይ መሥራት ያስፈልጋል ሲሉ ምክትል ከንቲባዋ አስረድተዋል፡፡ በዘርፉ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የከተማ አስተዳደሩ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የአነስተኛና መካከለኛ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በሚፈለገው ደረጃ እንዳያድጉ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል የመሠረተ ልማትና የጥሬ ዕቃ ግብዓት እጥረት መኖር፣ እንዲሁም የኢንተርፕራይዞች ሽግግር ችግር መስተዋሉ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ", "passage_id": "66ff90a5e0ffcd69aca8791141b6acac" } ]
767ccf285c06c8758d641e136b630722
2b5be8284f231b7ecfc8a45403e518f0
ኢንስቲትዩቱ በአሥር ዓመቱ መጨረሻ ዓመታዊ የኤክስፖርት ገቢን 1ነጥብ2 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ እየሰራ ነው
ውብሸት ሰንደቁአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ ወደውጭ ከምትልካቸው የኬሚካልና ኢንዱስትሪ ግብዓት ዘርፍ ምርቶች በአስር ዓመቱ መጨረሻ ዓመታዊ የወጪ ንግድ ገቢዋን ከአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ለማድረስ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን የኢትዮጵያ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ሀላላ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፣ በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ከኤክስፖርት በዓመት አንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታስቧል። ይህንን ግብ ለማሳካትም በየዓመቱ በአማካኝ 120 ሚሊዮን ዶላር ከወጪ ንግድ ገቢ አፈጻጸም ማስመዝገብ ይጠበቃል፡፡የኤክስፖርት ሥራ በዋናነት ሀገሪቷ እየተጠቀመች ካለችው በላይ ማምረትን ይጠይቃል ያሉት አቶ ሳሙኤል፤ በኦጋዴን አካባቢ የተገኘው የተፈጥሮ ጋዝ በከፍተኛ ደረጃ ለኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ምርት ምቹ መሆኑ ለዕቅዱ ስኬት መልካም አጋጣሚዎችን እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ አስር ዓመታትም በዚህ ረገድ ከውጭ የሚገቡ ግብዓቶችን በአገር ውስጥ ከመሸፈን አልፎ በዕቅዱ ማጠናቀቂያ ዓመት ላይ የዘርፉ የኤክስፖርት ገቢ 1ነጥብ2 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡በቀጣይ አሥር ዓመታት የመሠረታዊ ኬሚካል የማምረት ሥራ የሚሠሩ ኢንዱስትሪዎችን የማስፋት ሥራ በትኩረት እንደሚሠራና ይህም ያላለቀላቸው ግብዓቶች ከውጭ እያስመጡ ከመሥራት ይልቅ የሀገሪቱን የማዕድናትና የግብርና ግብዓቶችን መሠረት የሚያደርጉ ትላልቅና መሠረታዊ ኬሚካሎችን በሀገር ውስጥ ማምረት ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ሥራ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ አቶ ሳሙኤል እንዳሉት፤ በስፋት ከፔትሮ ኬሚካል ውጤቶች የሚገኙ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ግብዓቶች የፕላስቲክ ወለል ንጣፎች፣ ፓይፖች እና የተለያዩ የቤቶች የማስዋቢያ ምርቶች በሀገር ውስጥ በስፋት እንዲመረቱ በትኩረት እየተሠራ ነው፡፡ በተጨማሪም የአፈር ማዳበሪያ የሀገር ውስጥ ፍጆታ ተሸፍኖ ኤክስፖርት ለማድረግ እየተሠራ ይገኛል፡፡ ፔትሮ ኬሚካል ጋር በተያያዘ የብዙ ምርት ግብዓት መሆን የሚችሉ ጥሬ ዕቃዎችን የማምረት ሥራም ትኩረት እንደተሰጠና ሌሎች የስፔሻሊቲ ኬሚካሎችንም ማምረት በመጀመር ሰፊ ኤክስፖርት አቅም እንዲኖራት ይሠራል፡፡ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በሀገሪቱ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ ያለ ኢንዱስትሪ ከመሆኑ ጋር ተያይዞም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ግብዓት አምራቾች በጥሩ ሁኔታ እያደጉ ያሉ ሲሆን፤ በሀገር ውስጥ የሲሚንቶ ምርትን መተካት እንደተቻለው ሁሉ ሌሎች የኮንስትራክሽን ዘርፉ ግብዓት የሆኑትን የእምነበረድ፣ የግራናይት፣ የቴራዞ፣ የጂብሰም እና የፊኒሽንግ ቁሶችን የማምረት አቅም በከፍተኛ ደረጃ እያደገ የመጣ ነው፡፡ አብዛኛው ለነዚህ ምርቶች ግብዓት የሚውለው ነገር ከሀገር ውስጥ የሚገኝ ስለሆነ እነዚህን ግብዓቶች ተጠቅሞ በስፋት ለማምረት በትኩረት ይሠራል፡፡ይህንን ግብ ለማሳካት ደግሞ በየዓመቱ በአማካኝ 120 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ከወጪ ንግድ ገቢ አፈጻጸም ማስመዝገብ እንደሚጠበቅ የታወቀ ሲሆን፤ ባለፉት አምሥት ዓመታትም 196 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያለው ምርት በኢንዱስትሪዎች መመረቱን እና ይህም በአማካይ ሲሰላ በየዓመቱ 39ነጥብ24 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው ምርቶች መመረታቸውን ከኢንስቲትዩቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 19/2020
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38348
[ { "passage": " ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ባለፉት አምስት ወራት 165 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ የውጪ ምንዛሪ ገቢ ማገኘቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በሚኒስቴሩ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ መላኩ ታዬ  ለኢዜአ እንዳስታወቁት ገቢው የተገኘው ከጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ ከቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ ካለቀላቸው የግብርና ምርቶች፣ ከፋርማሲቲካልና ኬሚካል ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ነው፡፡ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ22 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት በአገሪቱ እንዲስፋፋ መንግሥት ልዩና የተቀናጀ ድጋፍ በማድረግ ዘርፉን ይበልጥ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል የግብዓትና የምርት ትስስር የመፍጠር ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አቶ መላኩ ገልጸዋል፡፡የዘርፉን የሰው ኃይል ልማት ለማሳደግም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ከመካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ጋር የማቆራኘት ሥራ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል በአስተማማኝ መልኩ ለማልማት ከቴክኒክና ሙያ እንዲሁም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የማስተሳሰር ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍን ለማጎልበት መንግሥት የተለያዩ የፖሊሲ ድጋፎችን ያደረገ ሲሆን፤ በዋናነት የኢንቨስትመንት፣ የጉምሩክና የቀረጥ ማበረታቻ አዋጆች ተጠቃሾች ናቸው፡፡በተለይ ዘርፉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀጣይነት ባለው መልኩ ተወዳዳሪነቱን ለማጎልበት የሥራ አመራር ሥርዓት ሊያሰፍን የሚችል የካይዘን አሰራር በኢንስቲትዩት ደረጃ እንዲቋቋም መደረጉን አቶ መላኩ ገልጸዋል፡፡በተጓዳኝም የኢንዱስትሪ ዞን ልማት ስትራቴጂና የህግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ የማልማቱ ተግባር በመከናወን ላይ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመው፤  ዘመናዊ የቆዳና ሌጦ የግብይት ሥርዓት ሊያሰፍን የሚያስችል አዋጅ በረቂቅ ደረጃ መዘጋጀቱንም አመልክተዋል፡፡ ", "passage_id": "9d8aec8789be33097f1a8b27630c6cd8" }, { "passage": "በተያዘው አዲሱ የ2011 በጀት ዓመት የተሻለ ሰላምና መረጋጋት ይሰፍናል ተብሎ በመታመኑ፣ የፌዴራል መንግሥት ከወጪ ንግድ ዘርፍ 4.43 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ዕቅድ አወጣ፡፡በንግድ ሚኒስቴር ባለቤትነት የተዘጋጀው ይህ ግዙፍ ዕቅድ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ለሚመራው ብሔራዊ የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ ቀርቧል፡፡ ብሔራዊ የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ በ2010 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ከተገኘው 2.81 ቢሊዮን ዶላር ብልጫ ያለው ገቢ ለማግኘት በወጣው ዕቅድ ላይ ከመከረ በኋላ ያፀድቀዋል ተብሏል፡፡የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ዘርፍ በተለያዩ ችግሮች የተተበተበ በመሆኑ ላለፉት ዓመታት በዕቅድ መሠረት እየተጓዘ አይደለም፡፡ ነገር ግን የኤክስፖርት ዘርፍ ከነበረበት ችግር በተጨማሪ፣ ላለፉት ሦስት ዓመታት በኢትዮጵያ ተፈጥሮ የቆየው ቀውስ የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዲስተጓጎል በማድረጉ በዕቅዱ መሠረት መሄድ አልቻለም፡፡የንግድ ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያመለክተው በ2010 ግማሽ ዓመት ከወጪ ንግድ 2.2 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ቢታቀድም፣ የተገኘው ግን 1.35 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ በዋናነት የተመሠረተው በሦስት ዘርፎች ላይ ነው፡፡ እነዚህም የግብርና፣ የማኑፋክቸሪንግና የማዕድን ዘርፎች ናቸው፡፡ የወጪ ንግዱ በችግር የተተበተበም ቢሆንም የተወሰነ ዕድገት ያለው ሲሆን፣ ለአብነት ያህል በ2001 ዓ.ም. 1.45 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል፡፡ ከስምንት ዓመታት በኋላ በ2009 በጀት ዓመት የተገኘው 2.23 ቢሊዮን ዶላር ነው፡፡ በተለይ ላለፉት ሦስት ዓመታት የጠፋውን ሰላምና መረጋጋት መልሶ በማስፈን የተሻለ ገቢ ለማግኘት እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል፡፡የንግድ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የሰላም ጉዳይ በአገር ደረጃ ዋነኛ ሥራ ተደርጎ ተወስዷል፡፡ ዜጎች ተንቀሳቅሰው የሚሠሩበት ተገማች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲኖርና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ላለፉት አራት ወራት የተሠሩ ሥራዎች አሉ፡፡ ድርጅቱ [ኢሕአዴግ] በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉባዔ ያካሂዳል፡፡ ጉባዔው ከዚህ በፊት የነበሩ የሥራ አፈጻጸሞችን ተመልክቶ የሚያሳልፋቸው ውሳኔዎች ይኖራሉ፤›› በማለት የገለጹት አቶ መላኩ፣ ‹‹ውሳኔዎቹ ተግባራዊ ሲሆኑ የበለጠ መረጋጋት ይመጣል፡፡ ተቋማዊ አቅም እያደገ ይሄዳል፡፡ ተቋማዊ አቅሙ አሁን ካለበት ወደ ላቀ ደረጃ ይሸጋገራል፤›› ብለዋል፡፡አቶ መላኩ ጨምረው እንደገለጹት፣ በ2011 በጀት ዓመት የተሻለ ሰላም የሚሠፍን በመሆኑ የታሰበው የውጭ ምንዛሪ ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡     ", "passage_id": "7bab2938c3b1ecf5e8865308a4a4d7af" }, { "passage": "ባለፉት ስድስት ወራት የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የወጪ ንግድ ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር ማሽቆልቆሉ ተገለጸ፡፡የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ማክሰኞ ጥር 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት፣ ከማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ይገኛል ተብሎ ከሚጠበቀው 349 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ ሊገኝ የቻለው 198.5 ሚሊዮን ዶላር መሆኑን ገልጿል፡፡ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ አብተው ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት የስድስት ወራቱ የገቢ አፈጻጸም 56.5 በመቶ ብቻ ነው፡፡ከጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ ይገኛል ተብሎ ከታቀደው መገኘት የተቻለው 55.5 በመቶ ያህሉ ብቻ ሲሆን፣ ይኼም ካለፈው ዓመት በተመሳሳይ ወቅት በ0.5 በመቶ ቅናሽ ያሳየ መሆኑን፣ ከቆዳና የቆዳ ውጤቶች የገቢ ዕቅድ የተገኘው 50.4 በመቶ ካለፈው ዓመት 7.5 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡እንዲሁም ከሥጋ የወጪ ንግድ የገቢ ዕቅድ ሊገኝ የተቻለው 61.6 በመቶ ያህሉ ሲሆን፣ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ5.1 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል ብለዋል፡፡ሚኒስትሩ እንዳሉት፣ የወጪ ንግድ ገበያ መቀዛቀዝ በቆዳ ዘርፍ ለታየው የኤክስፖርት አፈጻጸም ጉድለት ተጠቃሽ ነው፡፡ በተመሳሳይ የጨርቃ ጨርቅ ዘርፉ በዓለም ገበያ መቀዛቀዝ ምክንያትና የተሻለ ትርፍ ፍለጋ የአገር ውስጥ ገበያ ላይ በማተኮሩ የገቢ አፈጻጸም ማሽቆልቆሉን ገልጸዋል፡፡የምክር ቤቱ የኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሰጠው አስተያየት ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ኢንቨስተሮች ገበያ ተኮር እንዲሆኑ ማበረታታትና የበለጠ ምርት በመላክ የተገኘውን ገበያ መጠቀም እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ", "passage_id": "9b608c1b40465d990b262bffad90f3a9" }, { "passage": "አገሪቱን በዓለም አቀፍ የንግድ ስርዓት ተወዳዳሪ በማድረግ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ መጠን ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን የንግድ ሚኒስትሩ ዶክተር በቀለ ቡላዶ ተናገሩ፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሁሉም ክልሎች ከተወጣጡ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር በ2009 አፈፃፀምና በ2010 እቅድ ዙሪያ በሃዋሳ ከተማ ምክክር እያደረገ ነው፡፡በምክክር መድረኩ ላይ ሚኒስትሩ ዶክተር በቀለ ቡላዶ እንዳሉት ሀገሪቱ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ተከትሎ ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ መዳረሻ እየሆነች ነው፡፡የወጪና ገቢ ምርቶችን የጥራት ቁጥጥርና ክትትል በማጠናከር ግልፅ፣ ፍትሃዊና በውድድር ላይ የተመሰረተ ዘመናዊ የንግድ ስርዓት በመዘርጋት ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች ላይ እሴት በመጨመር የአገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማስፋት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡በዋና ዋና ወጪ ንግድ አፈፃፀምም  ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የጥራጥሬ ምርቶች በመጠን 5 በመቶና በዋጋ 21 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡", "passage_id": "c3365ce31a0bb41630a9d8833b8d9f3d" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በወጪ ንግድ ዘርፍ ከታሰበው 95 በመቶውን ማሳካት መቻሉን ንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የ10 ዓመት መሪ ልማት እቅድ ዝግጅት ምዕራፍ እና የ2013 ዓ.ም እቅድ አፈፃፀምን ከክልል ከተማ አስተዳደር ንግድ እና ኢንዱስትሪ አካላት እንዲሁም ከተጠሪ አካላት ጋር እየገመገመ ይገኛል፡፡በዚህም ሚኒስቴሩ በንግድ ዘርፍ የፖሊሲ ማሻሻያ እና አሰራር ሪፎርም በሚያስፈልጋቸው ተቋማት ላይ ሰፊ ስራዎች በመስራት አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጿል፡፡በወጪ ንግዱም በሩብ ዓመቱ 95 በመቶ ያሳካ ሲሆን 839 ሚሊየን ብር የውጭ ምንዛሬ ማግኘቱንም አስታውቋል፡፡ከዚህ ውስጥ የግብርናው ዘርፍ 541 ሚሊየን ብር ወይም 73 በመቶ አፈፃፀም በማሳየት ቀዳሚው ነው ተብሏል፡፡የማምረቻው ዘርፍም 94 ሚሊየን ዶላር ያስገኘ ሲሆን የእቅዱን 95 በመቶ አሳክቷልም ነው የተባለው፤ የውጭ ምንዛሬ ድርሻውም 11 በመቶ ደርሷል፡፡የማዕድን ዘርፉ ከ205 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ገቢ 24 በመቶ የውጭ ምንዛሬ አስገኝቷል ነው የተባለው፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አምራች ዘርፉን ለማሳደግ ሰፊ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልፆ ለአብነትም ከአምስት ወራት በፊት ከፍተኛ የምርት እጥረት የታየበትን የሲሚንቶ ምርት ማሻሻሉን ገልጿል፡፡በዚህም በቀን 102 ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ ሲመረት የነበረውን አሁን ላይ በተደረገው ድጋፍ በቀን 310 ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ ማምረት መቻሉን አስታውቋል፡፡በመድረኩ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበልን ጨምሮ ሌሎች የተጠሪ ተቋምት ሃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡በፍሬህይወት ሰፊው", "passage_id": "7e2209f05e3635f167ee002e81f21927" } ]
97f6ce62d77972ffc38c996ee8a92557
3baeae6bc0e7371f526fa3a836911ec6
ለስፖርት ማህበራት የሚላኩ አመራሮች በግለሰቦች ትውውቅ መሆን የለበትም
የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ክልሎች ለሀገር አቀፍ ስፖርት ማህበራት የሚላኩ አመራሮች በግለሰቦች ትውውቅና በተወሰኑ አካላት ፍላጎት ብቻ መሆን እንደሌለባቸው አስታወቀ። የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እንደተናገሩት፤ ክልሎች ለሀገር አቀፍ ስፖርት ማህበራት አመራርነት የሚልኳቸውን ተወካዮች በተወሰኑ አካላት ፍላጎትና በግለሰቦች ትውውቅ መሆን የለበትም። በመሆኑም ለአመራርነት የሚላኩ ተወካዮች የተወከሉበትን ስፖርት ወደፊት ሊያሻግሩ ይችላሉ የሚለው በሚገባ ተተችቶ አሳታፊ በሆነ መልኩ ሊልኩ ይገባል ብለዋል። ለሀገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት የሚላኩ አመራሮች ምክንያታዊ አለመሆኑን ተከትሎ የሴቶችን በስፖርት ማህበራት የሴቶች ተሳትፎ ውስን እንዲሆን አድርጎታል። በሀገር አቀፍ ደረጃ 30 የስፖርት ማህበራት የሚገኙ ሲሆን በዚህ ውስጥ የሴቶች የአመራርነት ድርሻ ከ10 በመቶ አይበልጡም። ክልሎች በአብዛኛው የሚልኳቸው ዕጩ የሥራ አስፈፃሚ አባላት ወንዶች በመሆናቸው ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል። ሴቶች በተጨባጭ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ በየደረጃው የሚገኙ እና የአመራርነት ዕድሉን ያገኙ ሴቶች ማሳየት ችለዋል። በስፖርቱ ዘርፍ ግን ክፍተት የሚታይ መሆኑን የገለጹት አቶ ኤልያስ፤ «ኮሚሽኑ በቀጣይ በትኩረት ከሚሰራቸው ሥራዎች አንዱ ሴቶች በስፖርት አደረጃጀቶች ውስጥ በበቂ ሁኔታ በአመራርነት እንዲሳተፉ ማድረግ ላይ ይሆናል። ለዚህ ደግሞ ከክልሎች ጋር ከመነጋገር ባሻገር በመመሪያ እና በአሠራር የሚደገፍ ይሆናል» ብለዋል። የሴቶች የአመራርነት ተሳትፎ ቢያንስ 30 በመቶ ሊሆን እንደሚገባ የኦሊምፒክ ቻርተርን ጨምሮ የዓለም አቀፍ የስፖርት ማህበራት ሕጎች ያስቀምጣሉ። በኮሚሽኑ የስፖርት ማህበራት ስለሚቋቋሙበት ሁኔታ የአወጣው መመሪያ አንቀፅ 31 ንዑስ አንቀፅ 7 ይህን ሀሳብ የሚያጠናክር መሆኑን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። አዲስ ዘመን መጋቢት 18/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=29266
[ { "passage": "ብርሃን ፈይሳ በኢትዮጵያ ስፖርት፤ ማህበራትና ክለቦች ከመንግስት እገዛ አለመላቀቃቸውና ሃብት በማመንጨት ተግባር ላይ ተሳታፊ አለመሆናቸው እንደ ድክመት ይነሳል።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአጭር ጊዜ ውስጥ ፕሪሚየር ሊጉ በአክሲዮን ማህበር እንዲተዳደር በማድረግና ከጥገኝነት እንዲላቀቅ የማድረጉ ጅማሬም መልካም የሚባል ነው።ስፖርቱን በበላይነት በሚመራው ብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤትም የፌዴሬሽኑ ተግባር ለሌሎች ስፖርት ማህበራትም አርአያነት ያለው መሆኑ በሪፖርት ቀርቧል።ይሁን እንጂ ስፖርቱ በገቢ ረገድ ችግር እየደረሰበት መሆኑ ነው ፌዴሬሽኑ የጠቆመው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ\nፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ\nጂራ በመድረኩ ላይ\n፤ እግር ኳሱ\nበስፖንሰር ምክንያት እየደረሰበት\nያለውን ችግርና ችግሩ\nየተፈጠረበትን ምክንያት መንግስት\nማጤን ይኖርበታል ሲሉ\nገልጸዋል።ይኸውም በህዝብ ተወካዮች\nምክር ቤት የወጣውን\nየአልኮል መጠጦች ማስታወቂያ\nበህዝብ መገናኛ ብዙሃን\nእንዳይተላለፍና በስታዲየሞች \n ውስጥ እንዳይሰቀል የሚከለክለው አዋጅን በቀጥታ እግር ኳሱን የጎዳ መሆኑን ይጠቁማሉ።በእርግጥ መንግስት ዜጎቹን የመጠበቅ ኃላፊነት ይኑርበት እንጂ መታየት ያለባቸው ጉዳዮች ሳይመዘኑ ታልፈዋል የሚሉት አቶ ኢሳያስ፣ ‹‹ጉዳት አድርሶብናልና ቢፈተሽ›› ሲሉ ጥያቄያቸውን ለብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤቱ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ፌዴሬሽኑ ባለፈው ዓመት ከዋሊያ ቢራ ጋር 56 ሚሊየን ብር የስፖንሰር ስምምነት አድርጎ ነበር፤ ነገር ግን ይህ አዋጅ በወጣ ማግስት ስምምነቱ ተቋርጧል።በዓለም ላይ በሃብቱ ቀዳሚ የሆነው የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ በሃይንከን ቢራ ስፖንሰር እንደሚደረግ ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፤ ሌሎች ሊጎችም በመጠጥ አምራች ተቋማት ስፖንሰር የሚደረጉበት አሰራር በዓለም ላይ የተለመደ መሆኑን ጠቁመዋል።ፌዴሬሽኑ በዚህ ረገድ ያለውን ሃሳብ በጽሁፍ ለመንግስት ማቅረቡንና አዋጁ በፌዴሬሽኑ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረሱ በድጋሚ እንዲፈተሽ ካልሆነም መንግስት ብሄራዊ ቡድኖችን እንዲደግፍ ጠይቀዋል። እንደ ፕሬዚዳንቱ ማብራሪያ፤\nችግር ሲያጋጥም እርዳታ\nከማድረግ ባለፈ በኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን ስር\nካሉ የስፖርት ማህበራት\nመካከል ምንም ዓይነት\nድጋፍ ከማይደረግላቸው መካከል\nአንዱ የኢትዮጵያ እግር\nኳስ ፌዴሬሽን ነው።ፌዴሬሽኑ\nበስሩ ያሉትን ሰባት\nብሄራዊ ቡድኖችን (በሁለቱም\nጾታ በተለያየ የዕድሜ ክልል እና ዋናውን ቡድን ጨምሮ) በራሱ ነው የሚያስተዳድራቸው።ካሜሩን ለምታዘጋጀው የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን(ዋሊያዎቹ) ከማዳጋስካር፣ ኒጀር እና ኮት ዲቭዋር ጋር ተደልድሏል።በመሆኑም ቡድኑ የጉዞ፣ የሆቴልና ሌሎች በርካታ ወጪዎችን ማድረጉ የግድ ነው።በተመሳሳይ ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከዚምቧቡዌ እና ከጋና ጋር ባላት ድልድል ሌሎች ወጪዎችን ማድረግም ይጠይቃል።ሌሎቹ ብሄራዊ ቡድኖችም ለሚኖሯቸው አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ጨዋታዎች ተጨማሪ ወጪዎች ይጠበቃሉ።መንግስት ይህንን በባለቤትነት ወስዶ ብሄራዊ ቡድኖችን ሊያግዝ ይገባዋል። ብሄራዊ ቡድን ሃገር የምትወከልበት መሆኑ መንግስት ሊደግፈው ይገባሉ ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚካፈለው የአትሌቲክስ ቡድን በመንግስት እገዛ እየተደረገለት መሆኑን በማሳያነት ይጠቅሳሉ።ይህ የስፖርት ማህበራት ድክመት ደግሞ ብሄራዊ ቡድኑንም ደካማ አድርጎታል፤ በመሆኑም መንግስት ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል። አብዛኛዎቹ የእግር ኳስ ክለቦች የሚተዳደሩት በመንግስት እንደመሆኑ፤ ፌዴሬሽኑ ደግሞ ይህ መንግስት የሚመድበው ከፍተኛ ገንዘብ በዚህ መቀጠል የለበትም የሚል ሃሳብ እንደሌለው ገልጸዋል።ክለቦችን ወደ ግል ተቋም ለመመለስ በማቀድ ለሶስት ዓመታት ፕሮጀክት በመያዝ እየተንቀሳቀሱ ሲሆን፤ የመጀመሪያዎቹን ስድስት ወራት ከአንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ጋር በመሆን በትምህርት ቀጣዮቹን ጊዜያት ደግሞ 30 ከመቶ የሚሆኑትን ክለቦች 30 በመቶ መንግስት 40 በመቶ ህብረተሰቡ እንዲይዛቸው የግል ባለሃብት ተሳትፎ በማከል ሙሉ ለሙሉ ከመንግስት ለማላቀቅ ታቅዷል።በመሆኑም ምክር ቤቱ አንድ አቅጣጫ መስጠት እንደሚገባው አሳስበዋል፤ ይህ ካልሆነ ግን መንግስት ድጋፉን ቢያቋርጥ አስቸጋሪ ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ጠቁመዋል። ክልሎችም በስራቸው የሚያስተዳድሯቸው ክለቦች እንደመኖራቸው ለዚህ ስራ ተባባሪና በሚወጣው ደንብም ለመመራት እገዛ እንዲያደርጉም ፕሬዚዳንቱ ጠይቀዋል። በመድረኩ ላይ ሃሳባቸውን ያንጸባረቁት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሼር ካምፓኒ የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ፤ ባለፉት ዓመታት በሁለቱም ጾታዎች በዋናው ብሄራዊ ቡድንም ሆነ በእድሜ በተቀመጡት ቡድኖች የተደረጉት እንቅስቃሴዎች ደካማና አንገት የሚያስደፉ እንደሆኑ መታየታቸውን ይጠቁማሉ።ብሄራዊ ቡድኖች ሲያሸንፉ በተለያዩ የሃገሪቷ ከተሞች ላይ በህዝቡ ዘንድ የሚፈጠረው ተነሳሽነት ታይቷል። ሰብሳቢው አንድ ያልታተመ ጥናትን ዋቢ በማድረግ በ2011/12 ዓ.ም በስፖርቱ ወደ 2ነጥብ2 ቢሊየን ብር ወጥቷል፤ ነገር ግን ውጤት አልመጣም ይላሉ።በመሆኑም እግር ኳስ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት በዚህ መንገድ ይቀጥላል ወይስ ክለቦች ወደ ግል እንዲዘዋወሩና በገንዘብ ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ታቅዷል የሚለው መመልከት አስፈላጊ መሆኑንም ነው ሰብሳቢው ያመላከቱት። በእቅዱ ላይ ክለቦች ከመንግስት ተረጂነት ሊወጡ ይገባል በሚለው ላይ ፖሊሲ አውጥቶ ወደ ግል ይዞታነት የሚዘዋወሩበትን ስትራቴጂ መንደፍ አስፈላጊ ሲሆን፤ ተግባራዊነቱም ሊመዘን ይገባል። በዚህ ወቅት ከመንግስት ጥቂት መቋቋሚያ ቢያገኙ በአጭር ጊዜ ውስጥ ራሳቸውን የሚችሉና ከፍተኛ ደጋፊ ያላቸው ክለቦች መኖራቸውንም ሰብሳቢው ይጠቁማሉ።በመሆኑም ይህ ሊታሰብበትና በብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤቱ አቅጣጫ ሊሰጠው የሚገባ ነው ይላሉ። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ በ1990 ዓ.ም የወጣው የስፖርት ፖሊሲ ከስፖርት ማህበራትና ክለቦች አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ቀስ በቀስ ከመንግስት ድጎማ መውጣት እንዳለባቸው የሚያመላክት መሆኑን ይጠቅሳሉ።ይህንን ተከትሎ የተከናወኑ ስራዎች ቢኖሩም አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከጥቂቶቹ በቀር የተቀሩት በመንግስት የሚተዳደሩ ናቸው። ዓለም አቀፍ ደረጃቸው ሲፈተሽም፤ ከስያሜ፣ ከመዝሙር፣ ከአርማ፣… ጋር የተያያዙ ጉዳዮች መስተካከል ይገባቸዋል። ብሄራዊ ምክር ቤቱም ከዚህ ቀደም አቅጣጫ ቢያስቀምጥም ብዙም አልተሄደበትም።ክለቦቹም ከመንግስት ድጎማ በመውጣት ራሳቸውን እንዲችሉ ስልቶችን መቀየስ ይገባቸዋል።ለአብነት ያህልም የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎቹን ወደ አክሲዮን የቀየረበት መንገድ ገቢውን ከማሳደግ ጎን ለጎን የታዳጊ ቡድኖችን የያዘበት ጅማሮ የሚበረታታ ነው፡፡ ፌዴሬሽኖች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ ከማድረግ ባሻገር መንግስት በስሩ ያሉትን ከ30 በላይ ማህበራት ድጋፍ የማድረግ አቅሙ ውስን ነው።በመሆኑም ክለቦችና ስፖርት ማህበራት በራሳቸው ከሚያደርጉት ባሻገር ኮሚሽኑም ጥናት ላይ ተመስርቶ በቀጣይ የሚሄድበት መሆኑን ጠቁመዋል።  ", "passage_id": "36f13b967202258e302af2bc40e2da9c" }, { "passage": "የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ከተፈፀመ በኋላ የክለቡ ፕሬዝደንት አቶ አብነት ገብረ መስቀል እና የቦርድ አመራሮች አቶ ንዋይ እና አቶ ዳዊት ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች የሰጡትን ሰፊ ምላሽ አጠር ባለ መልኩ እንደሚከተለው አሰናድተን አቅርበነዋል።\nክለቡ ይፋ ስላደረገው ወደ አክሲዮን ሽግግር እቅድ አቶ አብነት፡ ይህ መነሻ ሀሳብ ነው ፤ ገና ውሳኔ አልተሰጠበትም፡፡ ይህም የአክስዮን ድርሻ ብዙዎችን እንዲያገል አይደለም የምንፈልገው፡፡ ሁሉም የሚታቀፍበትን መንገድ ነው እየፈጠርን ያለነው። ክለቡ በባላሀብት ብቻ ተይዞ የባለሀብቶች ክለብ ብቻ ሆኖ ሌላው ጊዮርጊስን ብሎ ፀሀይ ብርድ የሚቀጠቅጠውን ክለቡን እዚህ ያደረሰውን ህዝብ ትተን እንጓዝ ቢባል እኛም እሺ አንልም። ይህ ጥናት የቀረበው መነሻ ሀሳብ ነው አንድ ሚሊዮን የአክሲዮን መነሻ ሀሳቡ በዝቷል እታች ያለውን ደጋፊ አቅም ያማከለ አይደለም ከተባለ እንዴት አጣጥመን እንደምንሄድ ጥናቱን ካጠኑት ሰዎች ጋር ተነጋግረን በማስተካከል የምንሄድበት ነው የሚሆነው። አንድ ነገር መግለፅ የምፈልገው የአለም እግር ኳስ አደረጃጀት እየተቀየረ ነው የመጣው እኛም ራሳችንን ወደ ዘመኑ አሰራር እየከተትን ካልሄድን የትም አንደርስም፡፡ መቀየር አለበት አለበለዚያ ሌሎች ሀገሮች ከደረሱበት ደረጃ ሳንደርስ እኛም ሆንን ብሔራዊ ቡድን መፎካከር አንችልም ፤ ሀብት ሊኖረን ያስፈልጋል። ስለዚህ በዚህ መሰረት ታይቶ የክለቡን አቅም ልናሳድግ ይገባል። የኢትዮዽያ ወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስቴር እንዲሁም የኢትዮዽያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ክለቦች ራሳቸውን ችለው ሀብት የሚያሰባስቡበትን ህግ አሰራራቸውን ከልሰው በማየት አዲስ ማሻሻያ ህግ  ቢያስቀምጥ መልካም ነው።ከሌሎች የአፍሪካ ክለቦች የተወሰዱ ተሞክሮዎችአቶ አብነት፡ ከአንድም ሁለት ሦስት የአፍሪካ ክለቦች ፕሬዝዳንቶች ጋር አውርተናል ፤ ልምድም እየተለዋወጥን እንገኝለን፡፡ የግብፅ ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ዩጋንዳ አብዛኞዎቹ ሀገራት በመንግስት ባጀት ነው የሚተዳደሩት፡፡ የተወሰኑት ናቸው የህዝብ ክለቦች ያሉት። ሁሉም ነፃ መሆን ይፈልጋሉ ፤ አፍሪካ ስታድግ ስትበለፅግ በሁሉም ነገር የተሻለ ይሆናል። ክለቦች በራሳቸው የፋይናስ አቅም ሊመሩ ይገባል፡፡ አለበለዝያ ከሌሎች ሀገራት ጋር መፎካከር አስቸጋሪ ነው የሚሆነው ። የክለቡ  ወደ አክሲዮን ለመሸጋገር ከሀገሪቱ ህግ ጋር ማጣጣምአቶ አብነት፡ ይህ ለክለቡ ታሪካዊ እና ትልቅ ጉዞ ነው፡፡ መንግስት ፖሊሲውን ያሻሽላል ፣ ህጉን ይቀይራል፡፡ ይህን እኛ አናቀውም፡፡ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮዽያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አቶ ጁነይዲ ቅድም ሲናገሩ እንደሰማችሁት ሀሳቡን ስደግፉ ነበር። ይህ ሀሳብ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ብቻ አይደለም ለሀገራችንም ቢሆን ትልቅ አማራጭ በመሆኑ ወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስቴር የሚመለከታቸው አካላት ክለቦች ከመንግስት ድጎማ ተላቀው በራሳቸው አቅም እንዲመሩ መደረግ አለበት፡፡ ክለቦች የራሳቸው ሀብት ካላፈሩ እና ነፃ ሆነው ካልተንቀሳቀሱ ሲወርዱ እየፈረሱ ነገም ሌሎቹ ሲወርዱ የሚፈርሱ ከሆነ የእግር ኳሱ እድገት ምኑ ጋር ነው። እግርኳሱ የተረጋጋ ከመንግስት ድጎማ ፀድቶ ክለቦች ህዝባዊ መሆን አለባቸው፡፡ የዛሬው ቀን ለኢትዮዽያ እግርኳስ አይን መግለጫ ነው። መቼ ወደ ተግባር እንገባለን የሚለውን መጀመርያ ከመንግስት ቁጭ ብለን ጋር መነጋገር አለብን፡፡ ሌላው የደረሰበት ለመድረስ መንግስት ማነቆ መሆን የለበትም፡፡ የነበረው ህግ የድሮ የማህበራት ህግ ነው ፡ ስለዚህ ወደ ፕሮፌሽናሊዝም ለማምራት ከእነሱ ጋር እናወራለን። የታገዱትን አባላት ከክለቡ ስለማሰናበት አቶ ነዋይ፡ የሚገዛን የክለባችን መታደርያ ደንብ ነው፡፡ ይሄንንም በሚገባ መመልከት ያስፈልገናል።  መተዳደርያ ደንባችን በግልፅ ማን አባል እንደሆነ እና እንዳልሆነ አስቀምጧል፡፡ ምላዕተ ጉባኤውም በመተዳደርያ ደንባችን መሰረት መሟላቱን አረጋግጦ ተካሂዶል። ስለዚህ ይህንን ጠቅላላ ጉባኤ የጠራነው የአራት ሰዎችን ጉዳይ ወይም እነሱን ለማገድ አይደለም። ይህ ጠቅላላ ጉባኤ  ለአባላቱ ሊያደርስ የሚፈልጋቸው መልክቶች ነበሩ ያንንም በደንብ አድርሰናል። ከዚህ በላይ ለእኛ የጉባኤው ስኬት የምንለው የክለቡን አቅም ለማሳደግ ያቀረብነው ወደ ፊት ልናከናውናቸው የሚገቡ የ5 አመት እቅዳችን ነው። እርግጥ ነው ከጉባኤው እንደተነሳው ልናወያይ በዝርዝር ልንገልፅ ይገባን ነበር። ነገር ግን አጀንዳው ሰፊ በመሆኑ በዝርዝር መወያየት አልቻልንም፡ ይህን ወደ ፊት በስፋት እንመለስበታለን ።የክለቡ የቦርድ አመራር በአሰልጣኞች ስራ ላይ ጣልቃ ይገባል ስለመባሉአቶ አብነት፡ የቦርድ አባላት ከአሰልጣኞች ጋር ምንም ግኑኝነት የላቸውም፡፡ በአሰልጣኞች የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ ውስጥም ጣልቃ አንገባም ፤ ልንገባም አንችልም፡፡ አሰልጣኝ የምንቀጥረው አምነንበት ነው። ነገር ግን ያለፉትን አመታት ከውጭ የሚመጡ ተጨዋቾች በተመለከተ አሰልጣኞቹ የሚያቀርቡልንን ማፅደቅ ብቻ ነበር የኛ ስራ፡፡ ሆኖም የሚመጡት ተጫዋቾች እዚህ ሀገር ውስጥ ካሉት ተጨዋቾች በምንም ተሽለው ያልተገኙ ተቀያሪ ወንበር የሚቀመጡ ሲሆኑ እኛን ከደጋፊው ጋር እያጋጨ ሲሄዱ አንዳንዶቹ በምን ምክንያት ነው መርጠው ያስገቧቸው በሚል ከዚህ በኋላ ምርጫ ላይ ሄደን ማየት አለብን በሚል የተጫዋች ምርጫ ላይ እየተሳተፍን ነው። ደግሞም ድክመቶችን እየተመለከትን ዝም አንልም ዘንድሮ ክለቡን ወደ ከፍተኛ ደረጃ ለማድረስ ትልቅ እቅድ ስለያዝን ወደ ክለባችን በሚመጡ የሀገር ውስጥ ሆነ የውጭ ተጨዋቾች ምርጫ ላይ ተሳትፎ አድርገናል።የስታድየም ግንባታ አቶ አብነት፡ የስታድየሙ ግንባታ ከአክሲዮን ሽግግሩ ጋር ተያይዞ በውስጡ የተካተተ ስራ ነው። በዋናነት ትኩረት የሰጠነው አንዱም የስታድየም ግንባታውን ነው፡፡ የመጀመርያውም ስራችን እሱ እንዲሆን ነው የፈለግነው። ሌሎች የሄድንባቸው አካሄዶች አሉ ፤ መስመር ይዘዋል፡፡ ግን ሳያልቅ መናገር አያስፈልግም በሚል ነው በጠቅላላው ጉባኤ ላይ ሳንገልፅ የቀረነው። ነገር ግን የስታድም ግንባታውን በተመለከተ በዚህ የአክስዮን ኩባንያ ስናቋቁም እሱኑ የመጀመርያ ስራችን አድርገን ለማካተት አስበናል።የትጥቅ ጉዳዮችአቶ ዳዊት፡ እስከዛሬ የነበረው ወደ ኋላ መለስ አድርገን ያየነው ከሆነ የትጥቅ አጠቃቀማችን የተዘበራረቀ ነበር። ምክንያቱም ከመልካም ፍቃደኝነት ጋር ተያይዞ በአቶ አብነት ወጪ የሚሸፈን በመሆኑ በየአመቱ ከተለያዩ ድርጅቶች ምርቱ የሚመጣ ስለሆነ ዝብርቅርቅ ያለ ነበር። አሁን ግን ለሁለት አመት የሚቆይ የተሟላ ደረጃውን የጠበቀ ትጥቅ ለማምጣት የተለያዩ ጥናቶች ተጠንተው ለተጫዋቾቹም ለደጋፊዎቹም የሚሆን አንድ ወጥ ትጥቅ እንዲያቀርብልን ማክሮን ከተባለ ትልቅ የጣልያን ድርጅት ጋር ስምምነት ፈፅመናል። የዲዛይን መረጣው ተጠናቆ ወደ ምርት የሚገባ ነው የሚሆነው፡፡ በቀጣይ ባሉት ቀናት ውስጥ ወደ ጨዋታ ከመግባታችን ወይም ከገባን በኋላ ሊሆን ይችላል ሙሉ ትጥቁ ይገባል። ደጋፊውም የማልያው ዋጋው በዛ እያለ ነው፡፡ ያው ጥራት ላይ ያተኮረ እንዲሆን ታስቦ ነው ከስፖንሰሮች ጋር በመነጋገር ዋጋው ሊቀንስ የሚችልበትን መንገድ እንፈጥራለን።", "passage_id": "cdd0006eec4e5fe369ab2a1ede548d54" }, { "passage": "ስፖርት\nበስርዓት የሚመራ ውብ ክዋኔ መሆኑ ለተወዳጅነቱ በምክንያትነት ይጠቀሳል። ከአደረጃጀቱ ጀምሮ የትኛውም ዓይነት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የራሱ የሆነ ሂደትና ስርዓት አለው። ይህ ስርዓት ተጥሶ በዘፈቀደ ሲከወን ደግሞ የተወዳጅነቱን ያህል በአደገኛ አካሄድ ላይ ሊገኝ ይችላል። በኢትዮጵያ ስፖርት አደረጃጀት የሚስተዋለውም ይኸው ነው። የተቀመጠለትን አቅጣጫ በመሳቱም፤ ስልጠናው፣ ሰልጣኞች፣ ሃብት፣ ጉልበት፣ ጊዜ፣ … ለብክነትና ለአሰራር ድርርቦሽ ተዳርገዋል። ለውጤት ማጣትም የራሱን ሚና ሲጫወት ቆይቷል። በአገሪቷ ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን፤ የታዳጊ ማሰልጠኛ ፕሮጀክት፣ የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላት፣ አካዳሚዎች፣ ክለቦች እንዲሁም ብሄራዊ ቡድን የሚል መስመር በመዘርጋት እየሰራ መሆኑ ይታወ ቃል። ነገር ግን ይህ አሰራር በቅብብሎሽ ከመከናወን ይልቅ ሁሉም በራሱ መንገድና አካሄድ ሲመራው ቆይቷል። ይህም ለብክነት ምክንያት ሲሆን፤ ማሰልጠኛ ማዕከላቱ ሚናቸው ተመሳሳይ በመሆኑ የሰልጣኞች ሽሚያ እና የእርስ በርስ ቅሬታ ውስጥ እንዲገቡ ሲያደርጋቸው ቆይቷል። ይህንን የተመለከተው ኮሚሽኑ አገር አቀፍ ስፖርት ስልጠና ጣቢያዎች፣ ማዕከላትና አካዳ ሚዎች አደረጃጀትና ስርዓት መተግበሪያ ረቂቅ ሰነድ በማዘጋጀት፤ ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦችን በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። ረቂቁ አምስት ክፍ ሎች ያሉት ሲሆን፤ የመጀመሪያው ክፍል በማዕከ ላትና ፕሮጀክቶች መዋቅራዊ አደረጃጀት ላይ ትኩረቱን ያደርጋል። ቀጣዩ ክፍል ምዘና እና ውድድርን የሚመለከት ሲሆን፤ ሦስተኛው የሰል ጣኞችን የቅብብሎሽና ዝውውር፣ አራተኛው የባለቤትና ባለድርሻ አካላትን ተግባርና ኃላፊነት እንዲሁም በመጨረሻው ክፍል የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ስርዓትን የሚያጠቃልል ነው። የሰነዱ አስፈ ላጊነትም፤ በየደረጃው በሚገኙ ፕሮጀክቶች፣ ማሰል ጠኛ ማዕከላት፣ አካዳሚዎችና ክለቦች መካከል ወጥ እና ቅንጅታዊ አሰራርን መዘርጋት ነው። በዚህም መሰረት ለሁሉም የየራሳቸው የሆነ የአሰራር ስርዓት ተበጅቶላቸዋል። በየአካባቢውና ትምህርት ቤቶች ከ13ዓመት በታች (11እና12) በሆነ ዕድሜ ስልጠናው የሚጀመር ሲሆን፤ በዚህም በርካታ ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎችን በተመሳሳይ ዕድሜ ማግኘት ይቻላል። ሁለት ዓመታትን በሚሸፍነው በዚህ ስልጠናም በዋናነት ሥራው የተሰጥኦ ፍለጋ ይሆናል። በቀጣይም ታዳጊዎቹ በ15 ዓመት በታች (13እና14) የስልጠና ጣቢያዎችን በመቀላቀል ለሁለት ዓመታት ይሰለጥናሉ። በዚህ የተሰጥኦ ልየታ ወቅትም ከአሰልጣኞቻቸው እገዛ ባሻገር በምዘና ያላቸውን ተሰጥኦ ለመለየት ይቻላል። በ17\nዓመት በታች (15እና16) ወደ ስልጠና ማዕከላት በመግባት የተለየውን ተሰጥኦአቸውን ማልማት የሦስት ዓመታት ሥራ ይሆናል። በዚህ ወቅት የስልጠና ጫናን የመሸከም ብቃታቸው የሚ መዘን ሲሆን፣ በማዕከላት መካከል የሚደረገውን ውድድር ጨምሮ በአገር አቀፍ ሻምፒዮናዎች እንዲሁም በዕድሜ በሚካሄዱ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተሳታፊ ይሆናሉ። ይህንን ሲያጠናቅቁ ወደ አካዳሚዎች የሚገቡ ሲሆን፤ ከ3- 4ዓመታት በሚዘልቀው ቆይታቸው ለኦሊምፒክ ብቁ እንደሚሆኑ ስለሚታመን ክለቦችን እንዲሁም ብሄራዊ ቡድኖችን ይቀላቀላሉ። የዚህ\nሂደት ባለቤቶችም የተለዩ ሲሆን፤ ከ13-17ዓመት በሚዘልቀው የስልጠና ወረዳ እና ዞኖች ኃላፊነት አለባቸው። የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላትን በባለቤትነት ክልሎች ሲያስተዳድሩ፤ አካዳሚዎች ደግሞ በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ስር ይገኛሉ። የትምህርት ሚኒስትር፣ የጤና ሚኒስትር፣ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ ወላጅ፣ አሰልጣኝ፣ ክለብ፣… ደግሞ ባለድርሻ አካላት እንደመሆናቸው ሥራውን በቅንጅት ያከናውናሉ። በዚህ ሂደትም ለዓመት ለሦስት ጊዜያት የመስክ ምልከታ፣ የብቃት ምዘና፣ ዓውደ ጥናት፣ ወቅታዊ ሪፖርት እና የዳሰሳ ጥናቶች እንደሚካሄድም ሰነዱ ይጠቁማል። ሰነዱ ገለጻ ከተደረገበት በኋላም ከተሳታፊዎች በርካታ አስተያየት ተሰጥቷል። የስልጠና ቁሳቁስ፣ የምግብ አቅርቦትና የላብ መተኪያ ላይ ቢታሰብበት፣ ሰልጣኞች ከክለቦች ብቻም ሳይሆን ከማናጀሮች ጋር በምን መልኩ ይሰራሉ፣ ወደ ውጭ አገራት ክለቦች የሚኖራቸው ዝውውር እንዴት ይሆናል፣ ስልጠናው ሳይጠናቀቅ ወደ ክለቦች የሚያደርጉት ዝውውር፣ በምልመላ ላይ መስፈርት ቢቀመጥ፣ እንደየ ስፖርት ዓይነቱ የምልመላ ዕድሜው ቢቀነስ፣ የስልጠናውን ጊዜ በዕድሜ ከመገደብ ይልቅ በሰዓት ማድረግ ቢቻል፣ ማስተግበሪያውን ወደ ሥራ ለማስገባት መመሪያ ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑ፣ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የስፖርት ማሰልጠኛ ሥፍራዎች አጠቃቀምን በተመለከተ፣ ማዕከላት ትኩረታቸውን በአትሌቲክስ ላይ ያደረጉ እንደመሆኑ የሌሎች እጣፋንታ ምን ይሆናል፣ እንደየ ደረጃው የአሰልጣኞች ደረጃ ቢወሰን፣… የሚሉ ሃሳቦች ተንጸባርቀዋል። በኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር ሲሳይ ሳሙኤል፤ ለሰነዱ ግብዓት የሚሆኑ አስተያየቶችን ማሰባሰቡ ቀጣይነት ያለው መሆኑን ይጠቁማሉ። ክልሎች፣ ፌዴሬሽኖች እን ዲሁም የሚመለከታቸው አካላት በአጠቃላይ አስተያየታቸውን በመስጠት ረቂቁ ዳብሮ ወደ ተግባር ይገባል። ይህ ሰነድ በትክክል ወደ ሥራ የሚለወጥ ከሆነም በስልጠናውና በአገሪቷ ውጤት ላይ ትልቅ ድርሻ እንደሚኖረውም እምነታቸው ነው። ሰነዱ ሲዘጋጅ በአገሪቷ ያሉትን የማሰልጠኛ ማዕከላትና አካዳሚዎች ልምድ እንዲሁም ጠን ካራና ደካማ ጎኖች በመያዝ ነው። ከዚህም ባሻገር በዘርፉ የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው አገራት እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ማዕከል እና አካዳሚ ለመባል መስፈርቶች በመነሻነት ተይዘዋል። አሰራሩ በወጥ አደረጃጀት፣ ደረጃ እና በተመሳሳይ አቅርቦት የሚካሄድ እንደመሆኑም በአንድ ቀን አዳር ይሳካል ለማለት እንደማያስደርም ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። ነገር ግን ማዕከላቱ በምን መልኩ መስራት እንደ ሚገባቸው ራሳቸውን ይመለከቱበታል፤ እንዲሁም ከዚህ በኋላ የሚከፈቱ የማሰልጠኛ ማዕከላት እንደ መስፈርት በመሆን የሚያግዛቸው መሆኑን አስረድተዋል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚ ሽነር ጌታቸው ባልቻ፤ ሰነዱ በዘርፉ በምን መልኩ ውጤታማ መሆን ይቻላል የሚለውን ለማመላከት የተዘጋጀ መሆኑን ይገልጻሉ። ከሰነዱ\nየሚጠበቀውም፤ ማዕከላት ተሳስረው ውጤታማ ሥራ በማከናወን በዓለም አቀፍ ደረጃ ውጤት ማግኘት ነው። በስፖርት ላይ በሚሰሩ አካላት 50ሺ እና ከዚያ በላይ የሆኑ ስፖርተኞች ሰልጥነዋል ይባላል፤ የሚታየው ግን ለአብነት ያህል በእግር ኳስ ስፖርት11 ተጫዋቾችን ማፍራት አለመቻሉን ነው። በርካታ የማሰልጠኛ ጣቢያዎችና ማዕከላት ኖሮን ሰልጥነው የሚወጡት ውጤት ማስመዝገብ ካልቻሉ አሰራሩንና አደረጃጀቱን ቆም ብሎ መመልከት አስፈላጊ ይሆናል። ይህ ሰነድ ዳብሮ ወደ ተግባራዊነት እንዲገባም ህግና መመሪያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች እንደሚኖሩም ምክትል ኮሚሽነሩ ይጠቁማሉ።አዲስ\nዘመን መጋቢት 16/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "47b43da4d0a7ec84c955c2256ff82e36" }, { "passage": "የክለቦች ደካማ አደረጃጀት በኢትዮጵያ የእግር ኳስ እድገት ላይ ትልቁ እንቅፋት እንደሆነ ይነገራል፡፡ ባለሙያዎቹ እንደሚሉት እነዚሁ ክለቦች «በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ» እንደሚባለው ብሂል አብዛኞቹ በመንግሥት ዳረጎት እየተሰፈረላቸው የሚተዳደሩ ናቸው፡፡ ከዚህም ሌላ እግር ኳሱ የተሻለ እድገት እንዲኖረውና ክለቦች ሕዝባዊ መሠረት እንዲላበስ የሚያስችል ስልት በፌዴሬሽኑ እና ስፖርቱን በሚመሩት ተቋማት አለመፈጠሩ ሌላው መሰናክል እንደሆነ የስፖርቱ ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡የዝግጅት ክፍላችን ባሳለፍነው ሳምንት የሊግ አደረጃጀት እና ክለቦች የሚገኙበትን ነባራዊ ሁኔታ በሚመለከት ሰፋ ያለ ዳሰሳ አድርጎ ነበር፡፡ በዚህ የእግር ኳስ ክለቦች ከአመሰራረታቸው አንስቶ በፖለቲካ ተፅእኖ ውስጥ የሚያልፉ መሆናቸው የሚያሳዩ መረጃዎችን ጠቃቅሰን አልፈን ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አብዛኞቹ ክለቦች በመንግሥት እና በልማት ድርጅቶች የሚተዳደሩ በመሆናቸው እራሳቸውን በፋይናንስ ሊደግፉ እና በነፃነት ሊመሩ የሚችሉበት ቁመና ላይ እንዳልሆኑ የሚያሳይ ጥናትም ጠቁመናል፡፡ የፋይናንስ ግልፅነት እና ተጠያቂነት ችግርም ሌላኛው የሊጉ የአደረጃጀት ፈተና መሆኑንም አንስተናል፡፡የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር ፊፋ ባስቀመጣቸው መለኪያዎች ሲቀመጡ አሁን ያሉት ክለቦች የክለብነት መስፈርት አያሟሉም፡፡ የስፖርታዊ፣ የመሠረተ ልማት፣ የአስተዳደርና የሰው ኃይል፣ የፋይናንስ እንዲሁም የሕጋዊ መስፈርቶችን ተከትሎ አገር ውስጥ ያሉ ክለቦችን ሲለኩ አብዛኛዎቹ «ክለብ» ለመባል የማይበቃ ደረጃ ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን ነው የተለያዩ ሰነዶች የሚያመለክቱት፡፡ በተጨማሪም አዲስ አደረጃጀት ማለትም የአክሲዮን እና የሊግ ካምፓኒ አደረጃጀትን ተረድቶ ተግባራዊ የማድረግ ዝግጁነት እንደሌላቸውም መረዳት ይቻላል፡፡ አንዳንድ የስፖርት ባለሙያዎች እንደ ዳንቴል የተወሳሰበውን የእግር ኳስ ፈተና በጥልቀት መታየት ይኖርበታል ሲሉ ምክረ ሃሳባቸውን ይሰነዝራሉ፡፡በዛሬው የእሁድ ገፅ የስፖርት አምዳችን ችግሮቹን ከላይ ጠቆም እንዳደረግነው ሁሉ በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ፊፋ ክለቦችን ለመመስረት እና ለማስተዳደር ምን ዓይነት መስፈርቶች ሊሟሉ ይገባል? የአገራችን ክለቦች ቁመና ከዚህ መስፈርት አንፃር ምን ደረጃ ላይ ይገኛል? የሚለውን ጉዳይ በስፋት እንዳስሳለን፡፡ ጉዳዩን በጉልህ ለማየት እንድንችል «FIFA club licensing Regulation» ወይም የፊፋን የክለቦች ፍቃድ አሰጣጥ እና ቁጥጥር ሕግ እንደ ማንፀሪያ እንጠቀማለን፡፡ዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር ፊፋ የክለቦች ፍቃድ አሰጣጥ እና ቁጥጥር ሥነ ሥርዓትን እንዲሁም መስፈርት ፈር የሚያስያዝ ሕግ በዋናነት ያወጣበት ምክንያት በአገር አቀፍ እና በኢንተርናሽናል ደረጃ የሚካሄዱ የሊግ ውድድሮችን በተሻለ ደረጃ እንዲከናወኑ፤ እግር ኳስ በማህበረሰቡ ውስጥ ተወዳጅነቱ ጠብቆ ዘላቂ እንዲሆን፤ ክለቦች የሚያንቀሳቅሱት ፋይናንስ ግልፅ አሠራር እንዲኖረው ለማድረግ፤ የክለቦቹ መስራቾች እና ባለቤቶች በግልፅ እንዲታወቁ እንዲሁም የቁጥጥር ሥርዓታቸው ግልፅ እንዲሆን ነው፡፡ በዚህ አግባብ ዓለም ላይ ውጤታማ የሆኑ የሊግ ውድድሮች እና ተሳታፊ ክለቦች ተፈጥረዋል፡፡ እግር ኳስም ከስፖርቶች ሁሉ ልቆ ተወዳጅነቱ በዓለም ላይ ግዘፍ ነስቷል፡፡ የአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ግን ከዚህ እውነታ ተቃራኒ ነው፡፡የአገራችን ክለቦች በፊፋ መስፈሪያ\nአንድን የእግር ኳስ ቡድን ክለብ የሚያሰኘውን ደረጃ የሚያሟላበት እና እግር ኳሱን በበላይነት ከሚመራው ፌዴሬሽን ፍቃድ የሚያሰጠው ስፖርታዊ መስፈርት ‹‹sport criteria›› አሟልቶ ሲገኝ ነው፡፡ የመጀመሪያው ስፖርታዊ መስፈርት ክለቦች ታዳጊዎችን የሚያፈሩበት ፕሮጀክት ሊኖራቸው እንደሚገባ የሚገልፅ ሲሆን በዚህ ውስጥ ታዳጊዎች በታክቲክ እና ቴክኒክ እንዲሁም በስነልቦና አንፆ ማፍራት ይኖርበታል፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ ከስፖርታዊ ክሎት በተጨማሪ የቀለም ትምህርታቸውን መከታተል እንዲችሉ ማመቻቸት እና መደገፍ ይኖርበታል፡፡ ከህክምና የማሰልጠኛ ሜዳን ጨምሮ የተለያዩ ስፖርታዊ ቁሶችንም በበቂ ሁኔታ ማሟላት ይኖርበታል፡፡ ታዳጊዎችን በዚህ መንገድ ቀርፆ ማውጣትም ክለቡ ለዋናው ቡድን መጠናከር ትልቅ መሠረት የሚጥል ነው፡፡ ለእግር ኳስ እድገትም ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ከላይ በጠቀስነው መስፈርት መሠረት አብዛኛዎቹን የአገራችንን ክለቦች ስንመለከታቸው እጅግ ወርደው እናገኛቸዋለን፡፡ ለይስሙላ በተለያየ የዕድሜ ደረጃ ያሉ ታዳጊዎችን በፕሮጀክት መንገድ አቅፈው ቢይዙም ነገር ግን ዓለም አቀፍ መስፈርትን ባሟላ መንገድ ለእግር ኳስ ፍቅር እና ፍላጎት ያላቸውን ታዳጊዎች የሚያንፅ ፕሮጀክት የላቸውም፡፡ በእርግጥ ይህን መሰል ፕሮጀክት ከፍተኛ ገንዘብ እና ፕሮፌሽናል ባለሙያ የሚፈልግ ቢሆንም ቅሉ የረጅም ጊዜ ውጤታማነትን አስበው ታዳጊዎችን ለማፍራት ጥረት ሲያደርጉ አይስተዋልም፡፡ በተለይ ክለቦች ለዋናው ቡድናቸው ተጫዋቾች የሚከፍሉትን ዓመታዊ ደመወዝ እና መሰል የተጋነኑ ወጪዎች ስንመለከት በእርግጥ ይህን ማድረግ ተስኗቸው ይሆን? የሚል ምፀታዊ ጥያቄ እንድናነሳ ያስገድደናል፡፡ በመሆኑም ፊፋ ባወጣው መስፈርት የታዳጊ ፕሮጀክት መስፈርት ስንመዝናቸው ደረጃ ውስጥ እንኳን ሊያስገባቸው የሚችል አቋም ላይ አለመሆናቸውን እንገነዘባለን፡፡ሌላኛው መስፈሪያ መሠረተ ልማት ነው፡፡ የተሟላ የስፖርት መሠረተ ልማት ለአንድ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ክለብ ዋናና አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይ ደረጃውን የጠበቀ የልምምድ እና የመጫወቻ ስታዲዮም ሊኖረው ይገባል፡፡ ከዚህ ጋር የታዳጊዎች ካምፕን ጨምሮ አስፈላጊ የሚባሉ የመሠረተ ልማት መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል፡፡ አሁን አሁን የስፖርቱ አፍቃሪ ማህበረሰብ ውድድሮችን በተሟላ እና ምቾት ባለው ስታዲዮሞች መመልከት ይፈልጋል፡፡ ገንዘቡን እና ጊዜውን ሲያፈስም ይህን ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ በመሆኑም ክለቦች የደጋፊዎቻቸውን እና የስፖርት አፍቃሪዎችን ፍላጎት ሊያሟላ በሚችል መንገድ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን ሊያሟሉ ይገባል፡፡በዚህ መመዘኛ የአገራችን ክለቦች የት ደረጃ ላይ ናቸው ብለን ስንጠይቅ አሁንም የምናገኘው ምላሽ ‹‹እጅግ ዝቅተኛ ነው›› የሚል ነው፡፡ በቂ ገበያ የማፈላለግ እና የፋይናንስ አቅም የማጠናከር ሥራ ሰርተው የተሟላ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን የማከናወን አቅም ያላቸው አይደሉም፡፡ የግል ንብረታቸው የሆኑ ስታዲዮሞች የላቸውም፡፡ በጣት በሚቆጠሩ ክለቦች ጅምር እንቅስቃሴዎች ቢኖሩም ቅሉ ሁሉም መንግሥት በገነባቸው ሜዳዎች ላይ ነው ጨዋታዎቻቸውን የሚያካሂዱት፡፡ ይሄም ቢሆን ፊፋ ባስቀመጠው ዘመኑን የሚመጥኑ ሜዳዎች ደረጃ ስንመለከተው ለልኬት እንኳን የማይመጥን ሆኖ እናገኘዋለን፡፡አፈር እና ድንጋይ ብቻ በሞላቸው ሜዳዎች ላይ የሊግ ውድድሮች ይካሄዳሉ፡፡ ይሄ ደግሞ የክለቦቹንም ሆነ የሊጉን ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዳው ይገኛል፡፡ በተለይ እግር ኳሱ አንድ ቦታ እንዲቆም እና እንዳያድግ እንደምክንያት ከሚጠቀሱት ውስብስብ ችግሮች መካከል የስፖርት መሠረተ ልማት ቀዳሚውን ይዛሉ፡፡ እንደ አገር በዚህ ዘርፍ ላይ እየተሰራ ያለው ክንዋኔ እንደ በጎ ጅምር ቢወሰድም በክለቦች ደረጃ ግን እጅግ ዝቅተኛ ነው፡፡ሦስተኛው የክለቦች መመዘኛ መስፈርት ‹‹የክለብ አስተዳደር እና አመራር›› ነው፡፡ አሁን አሁን የእግር ኳስ ክለቦች ከስፖርታዊ እንቅስቃሴያቸው በላይ ትልቁን ትኩረት የሚስቡት በሌሎች አትራፊ ሥራዎች ላይ መሰማራታቸው እና አቅማቸውን ማጎልበታቸው ነው፡፡ዓለም ላይ ስኬታማ የሆኑ ክለቦች አስተዳደራቸው ጠንካራ በመሆኑ ኢኮኖሚያቸውን እጅግ ሲያፈረጥሙ እና የስፖርቱን ደረጃ ዙሩን በማክረር ሲመሩት እንመለከታለን፡፡ የገበያ ስልታቸው እጅግ ጠንካራ ከመሆኑም ሌላ የፋይናንስ፣ የመዝናኛ እና የሚዲያ ክፍሎችን በማጠናከር የክለቦቻቸውን ኃያልነት እና ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ሥራ ይሰራሉ፡፡ ከሁሉም በላይ ግን የፋይናንስ ነፃነታቸውን ማወጅ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም በፕሮፌሽናል ደረጃ ተመዝግበው ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ ክለቦች አስተዳደራቸው በጠንካራ ባለሙያዎች እና አመራሮች የሚተዳደር መሆን አለበት፡፡\nበዚህ መስፈርት የምንቃኛቸው የአገራችን ክለቦች የሚገኙበት ደረጃ አሳዛኝ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ክለቦቹ በአማተር የሚመሩ እንዲሁም ብቁ ባለሙያዎች የሌላቸው ናቸው፡፡ ደካማ የገበያ ስልት የሚከተሉ እንዲያውም ከመንግሥት ተመፅዋችነት ያልተላቀቁ ናቸው፡፡ በተለይ በርካታ ደጋፊ ያላቸው ክለቦች አጋጣሚውን ወደገበያ ቀይረው እራሳቸውን ማጠናከር የተሳናቸው ናቸው፡፡ የእውቀትም የተነሳሽነትም ችግሮች በነዚህ ክለቦች ላይ ይስተዋላል፡፡ የመገናኛ ብዙኃን አጠቃቀማቸውም ዘመኑን ያልዋጀ ነው፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን አይችሉም፡፡ ውድድሮችን ለማድረግ የሚያስችል የግል አቅም አይፈጥሩም፡፡ ይህ ደግሞ ከላይ ለጠቃቀስናቸው ችግሮች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ አጋልጧቸዋል፡፡ለመጠቅለል\nፌዴሬሽኑ በአድራጊ ፈጣሪነት በሚመራው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ የሚገኙ ክለቦች የአመራርነት እና የውሳኔ ሰጪነት ሚናቸው ዝቅተኛ ነው፡፡ እግር ኳሱን እና የአገሪቷን ተጨባጭ ሁኔታ ታሳቢ የሚያደርጉ ሕጎች እና ደንቦችም አይዘጋጁም፡፡ ውድድሮች እንዴት እንደሚመሩ የሚያሳይ አጠቃላይ ሰነዶችም እንዲሁ፡፡ ይህ በተዘዋዋሪ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ ክለቦች እንዳይፈጠሩ እንቅፋት ሆኗል፡፡ በፊፋ የክለቦች ደረጃ አወጣጥ መስፈርት ስንመዝናቸውም ‹‹ክለብ ለመባል የሚያበቃ›› አቋም ላይ አይገኙም፡፡ ይባስ ብሎ አሁን ላይ እግር ኳስ ሜዳዎች እና ቡድኖች የብጥብጥ እና የስፖርታዊ ጨዋነት ጉድለት ዋንኛ ምሳሌዎች እየሆኑ ነው፡፡ ጭርሱኑ ‹‹ሳይቃጠል በቅጠል›› የሚባለው ይህን ጊዜ ነው፡፡አዲስ ዘመን ጥር 19/2011ዳግም ከበደ", "passage_id": "d74e599068673c3f4b45bb835a0c521e" }, { "passage": "ኢትዮጵያን ፕሮፌሽናል ፉትቦለርስ አሶሴሽን ዛሬ አመሻሽ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ባከናወነው ስብሰባ በተጨዋቾች ደሞዝ ገደብ ላይ ስለተላለፈው ውሳኔ ተቃውሞውን ገልፆ የራሱን ውሳኔ አስተላልፏል።ይጀመርበታል ተብሎ ከተነገረው አንድ ሰዓት ዘግይቶ የተጀመረው ስብሰባ ጥቂት ተጨዋቾች(10) የተገኙበት ነበረ። በቦታው ስብሰባውን በመምራት የማኀበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ግርማ፣ የማኀበሩ ፀሃፊ አቶ ሳምሶንን ጨምሮ ሶስት የስራ አስፈፃሚ አባላት ተገኝተዋል።በመጀመሪያ ሃሳባቸውን በመግለፅ ስብሰባውን የጀመሩት አቶ ግርማ በተደጋጋሚ ደብዳቤዎችን ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ልከው ምላሽ እንዳልተሰጣቸው እና ስብሰባውን የጠሩበትን ምክንያት አስረድተዋል። “ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ተገናኝተን ስብሰባዎችን አድርገን መግለጫዎችን አውጥተን ነበር። ነገር ግን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ምንም መልስ አልሰጠንም። ስለዚህ በቀጣይ ስለምንወስነው ውሳኔ ለመወያየት ይህንን ስብሰባ ልንጠራ ተገደናል። እኛ እንደ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የራሱን መታዳደሪያ ደንብ፣ የፊፋን መተዳደሪያ ደንብ እና የኢትዮጵያን የፍትሃቤር ህግን የጣሰ ድርጊት አድርጓል ብለን እናምናለን።” በማለት በነሱ በኩል ፌደሬሽኑ ጥሷቸዋል ያሏዋቸውን ነጥቦች መዘርዘር ቀጥለዋል።አቶ ግርማ በገለፃቸው ከፌደሬሽኑ ጋር ውሳኔው እንዲወሰን ያደረገው አካል (የስፖርት ኮሚሽን) በፌዴሬሽኑ መተዳደሪያ ደምብ መሰረት የፌደሬሽኑ አባል አለመሆኑ፣ በፌደሬሽኑ ደምቡ ላይ የተገለፀው የአባላት (ተጨዋቾች) መብት አለመጠበቁ ፣ አንቀፅ 47 ላይ የተደነገገው የስፖርት ግልግል ጉባኤ አለመተግበሩ ጉዳዩን ህጋዊ እንደማያደርጉት አስረድተዋል። አቶ ግርማ በንግግራቸው ማብቂያም እስከ ሐሙስ (መስከረም 01) ድረስ ፌደሬሽኑ መልስ ካልተሰጣቸው ጉዳዩን ወደ ህግ ቦታ (ፍርድ ቤት) እንደሚወስዱት ጠቁመዋል።በመቀጠል የአሶሴሽኑ ፀሃፊ አቶ ሳምሶን ተጨማሪ ሃሳብ ሰተዋል። “ምክትል ፕሬዝዳንታችን እንደገለፀው ለፌደሬሽኑ ጥያቄያችንን አስገብተን መልስ እየጠበቅን ነው። እኛ አሁንም ከፌደሬሽኑ ጋር ለመስራት ፍቃደኞች ነን። ግን በዚህ ዓይነት መልኩ አይደለም። የፌደሬሽኑ ዋናው ክፍሎች ተጨዋቾች ናቸው። ፌደሬሽኑም የተጨዋቾችን መብት ማስጠበቅ አለበት። ይህንን ሳያደርግ፣ ተጨዋቾች ሳያማክር እና መግለጫ ሳይሰጥ ውሳኔ ማሳለፍ ትክክል አይደለም።” በማለት ሀሳባቸውን ከገለፁ በኋላ በአምስቱ ቀናት (እስከ ሐሙስ) ፌደሬሽኑ እነሱን ለማነጋገር ከፈለግ በራቸው ክፍት እንደሆነ አስረድተዋል።መድረኩን ሲመሩ ከነበሩት ስራ አስፈፃሚዎች ኤፍሬም ወንድወሰን በመጨረሻ ተጨማሪ ሃሳብ ሰንዝሯል። “ይሄ ማህበር ከተመሰረተ ጀምሮ አላማውን ለማሳካት እኛ የምንችለውን እያደረግን ነው። በዋናነት አላማችን የተጨዋቾችን መብት ማስከበር ነው። ከዚህ ቀደም ተጨዋቾች ላይ ሲደርሱ የነበሩ የተለያዩ የመብት ጥሰቶች ነበሩ። አሁን ግን ከመንግስት የተሰጠን ፍቃድ በመጠቀም የመብት ጥሰቶችን ለመከላከል እንሰራለን። እኛ ፍቃድ ካገኘን በኋላ ግን እኛን ያላማከለ ውሳኔ ተወስኖ የሞራል ጉዳት ደርሶብናል። እንደተባለው በተደጋጋሚ ለፌደሬሽኑ ጥያቄዎችን ብናስገባም ዝም ስለተባልን ካሉን የህግ ሰዎች ጋር ተመካክረን ቀጣይ መንገዳችንን ወስነናል። በዚህም ሁላችንም ወደምንዳኝበት ፍርድቤት ጉዳዩን ይዘን እንሄዳለን።” ብሏል። ኤፍሬም ጨምሮም ተጨዋቾች እና ክለቦች በጉዳዩ ግራ እየተጋቡ መሆኑን አስረድቷል።ከሶስቱ የአሶስሽኑ ስራ አስፈፃሚዎች ገለፃ በኋላ በቦታው ለተገኙ ጥቂት(10) ተጨዋቾች ሃሳብ እንዲሰጡ ዕድል ተመቻችቶ ነበረ። ነገር ግን በቦታው የተገኙ ተጨዋቾች ሃሳብ ሳይሰጡ በቀጥታ ከብዙሃን መገናኛዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ መሰጠት ተጀምሯል።አቶ ግርማ\n“ልክ ነው ብዙ አባላቶቻችን አልተገኙም። ያልተገኙበት ምክንያት ደግሞ ብዙ ሊሆን ይችላል። የእኛም ድክመት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ዛሬ የቡድን አምበሎችን ብቻ ነው የጠራነው። እንደሚታወቀው ደግሞ በሀገራችን ብዙ የክልል ክለቦች አሉ። ስለዚህ እነሱ ካሉበት ቦታ ለመምጣት አልቻሉ ይሆናል። ከምንም በላይ ግን እኛ ገና ጀማሪዎች ስለሆንን እና ተጨዋቾች ስብሰባ ላይ የመገኘት ብዙም ልምዱ ስለሌላቸው ይሆናል ዛሬ ያልተገኙት።”“እኛ የምንከሰው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽንን ነው። ከክለቦች ጋር ምንም ችግር የለብንም። ክለቦቻችን ምንም አድርገውናል ብለን አናምንም። ከዚህም ቀደም የተጣላንበም ሆነ ወደ ህግ ቦታ የተዳረስንበት ነገር የለም። እርግጥ እስከ አራት ወር ደሞዝ ያልተከፈላቸው ተጨዋቾች ቢኖሩም ክለቦችን በትዕግስት እየጠበቁ ነው። ስለዚህ እኛ የምንከሰው ኋላ ቀር አሰራር የሚከተለውን እና የራሱን መተዳደሪያ ደምብ አገላብጦ ያላነበበውን ፌደሬሽናችንን ነው።”“ማኅበራችን ድሮ ነበረ መቋቋም የነበረበት። በዋናነት አላማችን ኢትዮጵያ ውስጥ ፕሮፌሽናሊዝምን ማምጣት ነው። ምክንያቱም በአማተር ሰዎች ነው እግር ኳሳችን እየተመራ ያለው ይህንን ደግሞ መቀየር አለብን። ስለዚህ ዋና አላማችን ይህ ነው። ከዚህ በተጨማሪ የሃገራችንን እግር ኳስ ለማሳደግ የሚጠቅሙ ዓላማዎችን ይዘን ነው የተቋቋምነው።”ኤፍሬም ዘካሪያስ“ማህበሩን ለመመስረት ረጅም ጊዜ ወስዷል። ከሦስት ዓመት በፊት የተጨዋቾችን ማህበር ለማቋቋም ፈልገው ፍቃድ ለመውሰድ የተንቀሳቀሱ ሰዎች ተከልክለው ነበረ። በዛን ሰዓት እየተጫወቱ ስላልሆነ። አሁን ግን ህጉ እንደ አዲስ ከተከለሰ በኋላ እኛ ሄደን ማህበሩን ተባብረን በህጋዊነት አቋቁመናል። እኛ ማህበራት እና በጎ አድራጎት ኤጀንሲ ሄደን ያለውን መመዘኛ አሟልተን ነው የተቋቋምነው ፤ ስለዚህ ህጋዊ ነን። በፕሬዝዳንትነት እና ምክትል ፕሬዝዳንትነት የተመረጡትም ሰዎች በጠቅላላ ጉባኤው አማካኝነት የተመረጡ ናቸው። ሁሉም ነገር በህጋዊ መንገድ የተደረገ ስለሆነ ምንም ጥያቄ የሚያስነሳ አይሆንም። እኛም እዚህ ቦታ የመጣነው ለሳንቲም ብለን አይደለም። ሙያውን ለማስከበር እንጂ። ስለዚህ ዋናው ነገር የሙያው ክብር ነው።”", "passage_id": "8736cd309e483248a698045f1758a319" } ]
53365e7e932af319fd569f726b34402b
f2cbdfb95e91f0871fe0229ac9269f50
“ በእነዚህ ፈታኝ ጊዜያትም እንኳ፣ ዘላቂ ሰላም እውን እንዲሆን የዜጎችን እና የተቋማትን የቅርብ ተሳትፎ የሚፈልጉ በርካታ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- በእነዚህ ፈታኝ ጊዜያትም እንኳ፣ ዘላቂ ሰላም እውን እንዲሆን የዜጎችን እና የተቋማትን የቅርብ ተሳትፎ የሚፈልጉ በርካታ ርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለጹ:: ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገጻቸው እንዳስታወቀቁት፤ የአስር ዓመቱ ብሔራዊ የልማት እቅድ ፍኖተ ብልጽግና ዘላቂ ሰላምን በሚያመጣ የልማት ጉዞን መሰረት ያደረገ ነው::ዘላቂ ሰላም እውን እንዲሆን ደግሞ የዜጎችን እና የተቋማትን የቅርብ ተሳትፎ የሚፈልጉ በርካታ ርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ:: “ልማት ዘላቂ ሰላምን ያመጣል። የ10 ዓመት ብሔራዊ የልማት ዕቅድ ፍኖተ ብልጽግና ይህንን ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው፤” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዕቅዱ ሰላምን እና የሕግ የበላይነትን ወሳኝ ግቦች አድርጎ ማስቀመጡ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል:: አያይዘውም፣ “በእነዚህ ፈታኝ ጊዜያትም እንኳ፣ ዘላቂ ሰላም እውን እንዲሆን የዜጎችን እና የተቋማትን የቅርብ ተሳትፎ የሚፈልጉ በርካታ ርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ፤” ሲሉ ገልጸዋል።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38376
[ { "passage": "ኮቪድ-19 በዜጎች ጤና ላይ እያሳደረ ያለውንና ወደ ፊትም የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለማስቀረት እና የወረርሽኙን ስርጭት ለመግታት የኢትዮጵያ መንግስት የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰደ ነው። በመንግስት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች በዋናነት አካላዊ ንክኪን ማስወገድ እና ማህበራዊ ፈቀቅታን ማስጠበቅን ዓላማ ያደረጉ ናቸው። እነዚህ እርምጃዎች በእርግጥ ወረርሽኙ በሰው ጤና ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ብሎም ስርጭቱን ለመግታት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው። \nእርምጃዎቹ ወረርሽኙን ለመከላከል የሚኖራቸው አስተዋጽኦ የማይካድ ቢሆንም በዜጎች የዕለተ ዕለት ኑሮ ላይ የሚያሳድሩት ጫናም ቀላል የማይባል ነው። በተለይም በዕለት ገቢ የሚተዳደሩ፣ ቋሚ ገቢ የሌላቸው እና የድሃ ድሃ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚያጋጥማቸው ጉዳት የከፋ ሊሆን እንደሚችል ጥናቶች አመላክተዋል።\nወረርሽኙ በስራ ስምሪት እና በኢኮኖሚ እድገት ላይ ሊኖረው የሚችለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመረዳት የተደረጉ ጥናቶች እንዳመላከቱት ወረርሽኙን ለመከላከል የሚወሰዱ እርምጃዎች በዋናነት ዝቅተኛ ገቢ ባለው ማህበረሰብ እና በኢ መደበኛ ዘርፍ የተሰማራ የህብረተሰብ ክፍል ላይ ከባድ ጫና ይኖረዋል።\nበፕላንና ልማት ኮሚሽን የመሪ ፕላን ዝግጅትና ጥናት ዳይሬክተር እና የጥናት ቡድኑ አባል አቶ ሃብታሙ ታከለ እንደገለጹት አሁን በወረርሽኙ ሥጋት ምክንያት የኑሮ ሁኔታቸው ተገላጭ የሆኑ 15 ሚሊዮን ዜጎች የዕለት ደራሽ የምግብ እርዳታ ማቅረብ እንደሚያስፈልግ ጥናቱ አመላክቷል። ከነዚህ ውስጥ ጥቃቅን ኢ-መደበኛ ንግዶች ላይ የተሰማሩት ተጠቃሽ ናቸው።\nኢኮኖሚው ወደ ታች እንዳይንሸራተት መንግስት ከሚያደርገው ጥረት ባሻገር እነዚህ ዜጎች የከፋ ችግር ውስጥ እንዳይገቡ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ መሆኑን ጥናቱ አመላክቷል። በጥናቱ በተመላከተው መሰረትም መንግስት ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን የተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች የዕለት ደራሽ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ መንግስት ባለው አደረጃጀት፣ በጀትና ባቋቋመው ኮሚቴ አማካኝነት የምግብ ክምችት የማዘጋጀት ስራ እየሰራ ነው።\nበወረርሽኙ ምክንያት እርዳታ የሚፈልጉ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመለየትና ችግሩ እስከ ሶስት ወር ቢቆይ ለተለዩት እርዳታ ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ፍላጎቶችን የመለየት ስራ መሰራት እንዳለበት በጥናቱ ተመላክቷል።\nመደበኛ ባልሆነው የሥራ መስክ የተሰማሩና ወደ ድህነት በቀላሉ ሊንሸራተቱ የሚችሉ ዜጎችን ጨምሮ፣ በከተማ ሴፍቲኔት ታቅፈው የሚደገፉ ዜጎች፣ እንዲሁም ከሥራ ገበታቸው ሊቀነሱ የሚችሉ በጉልበት ሥራ የተሰማሩና የጎዳና ተዳዳሪዎችን ቢያንስ በምግብ እንዳይጎዱ ለመደገፍ ተጨማሪ በጀት መመደቡን አስረድተዋል። ዜጎች የምግብ ድጋፍ የሚያገኙበት ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል።\nእንደ አቶ ሀብታሙ ማብራሪያ፤ በየአካባቢ የምግብ ባንኮች ተዘጋጅተው በመንግስት እያደረገ ካለው ጥረት በተጨማሪ በየአካባቢው የምግብ ባንኮችን በማዘጋጀት አቅም ያላቸው ዜጎች አቅም ለሌላቸው ድጋፍ የሚያበረክቱበት ሁኔታ ተመቻችቷል። አቅም ያላቸው ዜጎችም እጅግ አበረታች ድጋፍ እያደረጉ ናቸው። የምግብ ባንክ ምግብ የማሰባሰብ በታሰበው ሁኔታ እየተሰበሰበ ነው። ምግብ የማሰባሰብ ስራው በቀጣይ ጊዜያትም ይቀጥላል። አቅም ያላቸው ዜጎችም ድጋፋቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል።\nለተጋላጮች የምግብ ድጋፍ ለማቅረብ እና ለሌሎች ወጪዎች 1 ነጥብ 47 ቢሊየን ዶላር እንደሚያስፈልግ በጥናቱ መመላከቱን ያብራሩት አቶ ሃብታሙ የሚያስፈልገውን ሀብት የማሰባሰብ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከዚህ ውስጥ የተወሰነው ገንዘብ እስካሁን መገኘቱንም አብራርተዋል። \nለተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተደረገ ካለው እና ወደፊት ከሚደረገው የዕለት ደራሽ የምግብ እርዳታ በተጨማሪ ስራ ላይ ያሉ ዜጎች ከስራቸው እንዳይፈናቀሉ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ያብራሩት አቶ ሀብታሙ በወረርሽኙ ምክንያት ተቋማት ሰራተኛ እንዳይቀንሱ ተቋማት የባንክ ብድር የሚመልሱበት ጊዜ እንዲራዘምላቸው መደረጉን ጠቁመዋል። \nየኮሚሽነሯ አማካሪ እና የጥናት ቡድኑ መሪ አቶ አባስ መሃመድ በበኩላቸው፤ ለጊዜው ለተጎጂዎች ከሚደረገው ድጋፍ እጅግ ወሳኝ ነው። ነገር ግን በብዙ ሚሊየን ለሚቆጠሩ ዜጎች ድጋፍ እያቀረቡ መቀጠል አይቻልም። በመሆኑም በዋናነት እኮኖሚው በአስከፊ ደረጃ እንዳይንኮታኮት መስራት ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ መሆኑን ጥናቱ ማመላከቱ ገልጸዋል።\nኢኮኖሚው የበለጠ እንዳይደቅ የሚደረገው ርብርብ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በራሳቸው ሰርተው ራሳቸውን እንዲደጉሙ ለማስቻል እገዛ እንደሚኖረው የገለጹት አቶ አባስ፤ ኢኮኖሚውን ለመታደግ መንግስት ባለው አቅም ጥረት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ከተለያዩ ዓለም አቀፍ አጋር አካላትም ድጋፍ እየቀረበ መሆኑን አብራርተዋል።\nየቀድሞ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር እና በአሁኑ ወቅት በሀገረ ካናዳ በአማካሪነት የሚሰሩት ዶክተር ክበበው ኤርገኖ እንደሚሉት፤ ኮቪድ-19 ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ዜጎች ኑሮ ላይ የደቀነውን አስከፊ አደጋ ለመቋቋም መንግስት በዋናነት የዜጎች አፋጣኝ ፍላጎት ላይ ያነጣጠሩ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት መጀመሩ መልካም ነው።\nየዝግጅት ስራው ግን ተጠናክሮ መቀጠል አለበት የሚሉት ዶክተር ክበበው ወረርሽኙ ለወራት ሊቆይ ስለሚችል የሚደረገው ዝግጅትም በዚያ ልክ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ከዚያ ባሻገር ከአንድ የሀገሪቱ አካባቢ ወደ ሌላኛው አካባቢ የሚደረገው የሸቀጥ እና የምግብ ዝውውር እንዳይቋረጥም አስፈላጊው ክትትል ሊደረግ ይገባል ብለዋል።\nክልሎች የወረርሽኙን መዛመት ለመከላከል ወሰኖቻቸውን የሚዘጉ ከሆነ ከማንም በላይ ተጎጂ የሚሆነው ዝቅተኛው ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ነው ያሉት ዶክተር ክበበው፤ ከክልል ክልል እንዲሁም ከአዲስ አበባ ወደ ክልሎች የሚደረገው የሰው ምልልስ ቢቆም እንኳ የእህልና የሸቀጥ ምልል እንዳይቆም ማድረግ እጅግ ወሳኝ ነው ብለዋል።\nእንደ ዶክተር ክበበው ማብራሪያ እየተሰበሰበ ባለው የምግብ ክምችት ዙሪያ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ሊደረግ ይገባል። ለተጋላጭ ዜጎች የተሰበሰበው ምግብ እና ምግብ ነክ እቃዎችን ለሌላ ዓላማ ሊያውሉ የሚፈልጉ አካላት ላይ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 12 /2012 መላኩ ኤሮሴ", "passage_id": "274ccc593fde69b1b4aefaa6401c2796" }, { "passage": "የኢህአዴግ\nሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ትናንት ግንቦት 8 ቀን 2011 ዓም ባካሄደው ስብሰባ ባለፈው አንድ ዓመት የለውጥ ጉዞ ውስጥ የተከናወኑ የብሔራዊ ደህንነት ስኬታማ ስራዎችን እንዲሁም እያጋጠሙ ያሉትን ተግዳሮቶች የገመገመ ሲሆን የመፍትሄ አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል፡፡ ኮሚቴው\nየሀገራችንን ብሔራዊ ደህንነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ስራዎችን በጥልቀት የተመለከተ ሲሆን ለአብነትም በውጭ ሀገራት የነበሩ የታጠቁ ሃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ሃገር ውስጥ እንዲገቡ መደረጉ እንዲሁም ከኤርትራ ጋር የነበረው ሰላምም ጦርነትም ያልሆነ ግንኙነት መስተካከሉ ከለውጡ በኋላ የተገኙ ስኬቶች መሆናቸውን ግምግሟል፡፡ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በጸጥታና ደህንነት ተቋማት የሪፎርም ስራዎች መካሄድ መጀመራቸው፤ የደህንነት ተቋም አመራሮች ከፖለቲካ ወገንተኝነት የጸዱ እንዲሆኑ የሚያስችል የአመራር ለውጥ መደረጉን በጠንካራ ጎን የገመገመው የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የመከላከያ ሠራዊት ባለፈው አንድ ዓመት ጠንካራ ሪፎርም ካደረጉ ግንባር ቀደም ተቋማት አንዱ እንደሆነና ከአደረጃጀቱ ጀምሮ አጠቃላይ የመከላከያ መዋቅሩን ለማዘመን የሚያስችሉ ስራዎች መከናወናቸውንም አይቷል፡፡ ባለፈው\nአንድ ዓመት በአጠቃላይ በጸጥታው ዘርፍ ጠንካራ ስራዎች ቢከናወኑም በርካታ ተግዳሮቶች እያጋጠሙ መሆናቸው ኮሚቴው ገምግሟል፡፡ ተግዳሮቶቹ በዋናነት ከጽንፈኛ ብሔርተኝነት፣ ከኢ- መደበኛ አደረጃጀቶች ወይም ደቦዎች፤ ከህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር እንዲሁም ከማህበራዊ ሚድያ ሀሰተኛ ዜናዎች ተጽዕኖ ጋር የተያያዙ መሆናቸውንም ተመልክቷል፡፡ እነዚህ ተግዳሮቶች ለዜጎች ሞት፣ መፈናቀልና የደህንነት ስጋት ምክንያት መሆናቸውንም አስምሮበታል፡፡ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በብሔራዊ ደህንነት ጉዳይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡ በዚህም\nብሔራዊ ደህንነትን ማረጋገጥና የህግ የበላይነትን ማስከበር የመንግሥት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆናቸውን አፅንኦት በመስጠት የዜጎችን የሠላም ዋስትና የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ መረባረብ እንደሚገባ ውሳኔ አሳልፏል። ለደህንነት ተግዳሮቶች መነሻ ወይም ችግሩን በአጭር ጊዜ እንዳይቀረፍ ከማድረግ አንጻር ዋነኛው ችግር ያለው ከፖለቲካ ሥራ ጋር የተተያያዘ እንደሆነ በመለየት የደህንነት ሥራው ከፖለቲካ ሥራው ጋር ጎን ለጎን ተያይዞ እንዲሰራና በአንዱ የጎደለው በሌላው እየተሞላ አስተማማኝ ሰላም በአጭር ጊዜ ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ እንዲከናወን አቅጣጫ አስቀምጧል። ከአንዳንድ\nየአስተዳደር ወሰኖች ጋር በተያያዘ ሲስተዋሉ የነበሩ የጸጥታ ስጋቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መሻሻሎች ያሳዩ ቢሆንም ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ክልሎች ከክልሎች እና ክልሎች ከፌዴራል መንግሥት ጋር ስለሚኖራቸው ግንኙነት እንዲሁም የክልል የጸጥታ ሃይሎች ቅኝትና አወቃቀር በሚመለከት የሚስተዋሉ ችግሮች በህገ መንግስቱ መሰረት ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጠው ለማድረግ የሚያስችል ሥራ እንዲሰራ ኮሚቴው ወስኗል። የጸጥታ ኃይሎች ህዝባዊ ወገንተኝነታቸውን ባረጋገጠ መልኩ የዜጎች በሰላም የመኖርና የመንቀሳቀስ እንዲሁም ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው ለማስከበር በቁርጠኝነት እንዲንቀሳቀሱም አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት የየአካባቢያቸውን ሰላም ለማስከበር እንዲሰሩ ያሳሰበው ኮሚቴው ሰላም ወዳዱ ህዝብ እንደወትሮው ሁሉ ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ በንቃት እንዲረባረብ ጥሪውን አቅርቧል፡፡ ፍላጎትን በኃይል ለማስፈጸም የሚደረጉ አንዳንድ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት ሁለንተናዊ ርብርብ እንደሚያስፈልግም አስምሮበታል፡፡ ኮሚቴው\nየደህንነት ስጋት ምንጮችን በዝርዝር በመለየት ተግዳሮቶቹን በአጭር ጊዜ በመፍታት የተሟላ ሰላም ለማረጋገጥ በሚያስችሉ ዝርዝር ተግባራት ላይ ተወያይቶ የአፈጻጸም አቅጣጫ በማስቀመጥ ስብሰባውን ማጠናቀቁን የኢህአዴግ ም/ ቤት ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡አዲስ\nዘመን ግንቦት 9/2011በአስቴር\nኤልያስ ", "passage_id": "724e03f9522c2c71cf90a9f1aa49c232" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፦ የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን በመከላከል ረገድ በሁሉም ዘርፍ እየተሰራ ያለውን ውጤታማ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጥሪ አቀረቡ ። ወረርሽኙን መንግሥት ብቻውን መከላከል የማይችል በመሆኑ ህዝቡ ከመንግሥት ጎን ተሰልፎ በሽታውን እንዲከላከል አሳሰቡ:: \nየኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተቋቋመው ብሄራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ትናንት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በተለያዩ ንዑስ ኮሚቴዎች ሲሰሩ የቆዩ ሥራዎችን በመገምገም በቀጣይ መሰራት ባለባቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ አስቀምጧል። \nኮሚቴው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም፣ በጤና፣ በኢኮኖሚ፣ በትራንስፖርት፣ በቴክኖሎጂ፣ በውጭ ጉዳይ ላይ እና በሽታውን ለመከላከል እየተደረገ ካለው የድጋፍ አሰባሰብ ጋር ያሉ ሥራዎችን በሚመለከት ሪፖርት አድምጧል ። \nበወቅቱም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፤ በመንግሥት በኩል ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች እና በሽታውን ለመከላከል የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደው ለውጥ የመጣ ቢሆንም አሁንም በሚፈለገው ልክ እንዳልሆነ ተናግረዋል። \nለአብነትም የገበያ እና የትራንስፖርት አጠቃቀም ላይ ያለውን የህዝብ ጭንቅንቅ በማንሳት በሽታው የከፋ አደጋ ሳያስከትል በፍጥነት ማረምና ማስተካከል እንደሚገባ አመልክተዋል ። \nየጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በበኩላቸው፤ የላቦራቶሪ መመርመሪያ አቅምን ማሳደግ በመቻሉ አዲስ አበባን ጨምሮ በክልሎች 24 ላብራቶሪ እና 27\n መመርመሪያ መሳሪያ ስለ መኖሩ ጠቁመዋል።\nበቤት ለቤት ልየታ እስካሁን 3 ነጥብ 6 ሚሊዮን ቤቶች መጎብኘታቸውን እና በቤት ለቤት ልየታ አዲስ አበባ፣ ትግራይ እና አሮሚያ ክልሎች ጥሩ እንደፈጸሙ አስታውቀዋል ። \nእስከ ዛሬ ድረስ 133 በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ስለመገኘታቸው እና ከእነዚህ ውስጥ 66 ሰዎች ከቫይረሱ ስለማገገማቸው ተናግረዋል።\nየገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ በበኩላቸው ወረሽኙን ለመከላከል 15 ቢሊዮን ብር የበጀት ሽግሽግ እንደተደረገና በአጠቃላይ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ሀብት የማሰባሰበ ሥራ እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል ።\nበመደበኛ የነበረው 15 ሚሊዮን ተረጂ በኮቪድ-19 ምክንያት 15 ሚሊዮን ተጨምሮበት 30 ሚሊዮን ህዝብ እርዳታ የሚያስፈልገው በመሆኑ ይሄንን ችግር ለመፍታት በአዲስ አበባና በክልሎች የምግብ ባንክ መቋቋሙን አስታውቀዋል ።\nየሀብት ማሰባሰብ ንዑስ ኮሚቴ በክልል እና በፌዴራል እስካሁን ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር መድረሱን እና 40 ሚሊዮን የሚሆን ደግሞ በአይነት መገኘቱን የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል አስታውቀዋል። የምግብ ክምችት እና ስርጭት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።\nየኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም በበኩላቸው ፤በቦሌ አየር ማረፊያ በኩል ወደ አዲስ አበባ በቀን በአማካኝ የሚገቡ ሰዎች ቁጥር 30 ሰው ብቻ መሆናቸውን እና በአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ለ14 ቀናት የሚገቡ ስለመሆናቸው ገልፀዋል።\nአየር መንገዱ በጭነት አገልግሎት ጥሩ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንና በአትክልትና አበባ እንዲሁም በስጋ ምርቶች ላይ የትራንስፖርት ፍላጎት መጨመሩ ለአየር መንገዱ ገቢ እያስገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። \nጠቅላይ ሚኒስትሩ የእያንዳንዱን ዘርፍ የስራ እንቅስቃሴ ሪፖርት ካደመጡ በኋላ በሰጡት የሥራ መመሪያ፤ ኮቪድ-19 በመከላከል ረገድ በሁሉም ዘርፍ እየተሰራ ያለው ውጤታማ ሥራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል ። \nከጤና አንፃር ከኮቪድ-19 ውጪ ያሉ በሽታዎችንም በእኩል ሁኔታ የሚሰሩበት ሁኔታ መፍጠር እንደሚያስፈልግ አመልክተው ለዚህም የተቋማትን ምላሽ የመስጠት አቅምን መፈተሽ እንደሚገባ ተናግረዋል።\nአየር መንገዱ ከሌሎች አገሮች አንፃር ይሄ ነው የሚባል ድጋፍ ሳይደረግለት ራሱን ችሎ መቆሙን አድንቀው ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ማዕከል መሆኗን ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልፀዋል።\nአየር መንገዱ አገሪቱ በክፉ ጊዜ የምትጠቀምበት ብቸኛ አማራጭ በመሆኑ አቅሙን አጎልብቶ እየሰራ ያለውን ውጤታማ ሥራ ማጠናከር ይገባዋልም ብለዋል።\n‘’በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የመዘናጋት ሁኔታዎች ይስተዋላል’’ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት የወሰዳቸውን ርምጃዎች በትክክል ማድረስ እንደሚገባና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከመንግሥት ጎን ቆሞ ወረርሽኙን እንዲከላከል ጥሪ አቅርበዋል።\nህግ አስከባሪዎች የወጣውን አዋጅ በትክክል ማስተግበር እንዳለባቸውና ዜጎችም ለህግ ተገዥ እንዲሆኑ በማሳሰብ ጥቃቱን መንግሥት ብቻውን ሆኖ መመከት የሚችል ባለመሆኑ ህዝቡ ከመንግሥት ጎን ተሰልፎ በሽታውን እንዲከላከል መልዕክት አስተላልፈዋል።\nበትራንስፖርት በኩል ያለውን ችግር ለመፍታት የመንግሥት ተቋማት ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 24/2012", "passage_id": "1afbf787e8cabc4c7b0a37f24ba1c5e1" }, { "passage": "ዓለምን እያስጨነቀ ያለውና እስካሁን ከ20ሺ በላይ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመግታት በየአገራቱ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው፡፡ የሰዎችን እንቅስቃሴ ከመግታት ጀምሮ የሰዓት እላፊ የመጣል፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅና ሌሎች በርካታ እርምጃዎችም ተወስደዋል፤ እየተወሰዱም ይገኛሉ፡፡ ከዚህም ጎን ለጎን የተለያዩ ተቋማትም የየራሳቸውን እርምጃ ወስደዋል፡፡ ከነዚህ ውስጥ የሃይማኖት ተቋማት ይጠቀሳሉ::በኢትዮጵያም የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሃይማኖት አባቶች ለምእመኖቻቸው ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በተለይ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን በቤት ውስጥ መፈጸም እንዲሁም ንክኪን ማስወገድና እርቀትን በመጠበቅ የእምነት ተከታዮች እራሳቸውን ከበሽታው እንዲከላከሉ አስጠቅቀዋል። ያም ሆኖ ግን እስካሁን ባለው ሂደት የሃይማኖት ተከታዮች ከሃይማኖት አባቶችና ከጤና ሚኒስቴር የተላለፈውን መልዕክት ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ውስንነቶች እንደሚታዩ መታዘብ ችለናል፡፡ በተለያዩ እምነት ተቋማት አሁንም በተጨናነቀ መልኩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች እየተካሄዱ ናቸው፡፡ በአዳራሽ የሚካሄዱ የአምልኮ ሥርዓቶችም እየተስተዋሉ ነው፡፡የእምነት ተከታዮች የሃይማኖት መሪዎች፣ መምህራን፣ መንግሥትና የጤና ባለሙያዎች ያስተላለፉትን የጥንቃቄ መልዕክት ተግባራዊ እንዲያደርጉ፤ እራሳቸውንና ሌሎችንም ከበሽታው እንዲጠብቁ የሃይማኖት አባቶችና መምህራን በተደጋጋሚ ቢያሳስቡም በአግባቡ ወደተግባር መለወጥ አልተቻለም፡፡የእምነት መሪዎችና አባቶች በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ለምዕመናን ተደጋጋሚ የጥንቃቄ መልዕክት የማስተላለፍ ሥራ እየሰሩ መሆኑን የሚገልጹት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትንሳኤ ማተሚያ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አባ ንቡረዕድ ኤልያስ፤ በቤተክርስቲያኗ በኩል አንድ ሰው ከጥንቃቄ ጉድለት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሕይወቱ እንዳያልፍ ከእምነቱ አስተምሮ በመነሳት የእምነቱ ተከታዮች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በእምነት መሪዎች፣ አባቶች፣ መንግሥትና የጤና ባለሙያዎች የሚተላለፉትን የጥንቃቄ መልዕክቶች ተቀብለው ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሁንም ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን ነግረውናል፡፡«ለውጥ በአንድ ጊዜ የሚመጣ ባይሆንም ቫይረሱ የሰውን ሕይወት የሚቀጥፍና በፍጥነት የሚሰራጭ በመሆኑ ፈጣሪ በሰጠን እውቀት ተጠቅመን አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረጉ ተገቢ ነው» የሚሉት አባ ንቡረዕድ ኤልያስ፣ ምዕመናን ከቤተ ክርስቲያናት፣ ከእምነቱ አባቶችና ከቅዱስ ሲኖዶሱ እንዲሁም ከመንግሥትና የጤና ባለሙያዎች የሚያስተላልፉትን መልዕክት አስተውሎ በመፈጸም ገዳይ ከሆነው የኮሮና ቫይረስ ራስን መከላከል ይቻላል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል::የእስልምና ሃይማኖት መምህር ኡስታዝ አህመዲን ጀበል እንደገለጹት፤ የኮሮና ቫይረስ ጉዳይ የዓለም አጀንዳ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ብዙ አገራት እየፈተነና በሚያስደነግጥ ሁኔታ ብዙ ዜጎቻቸውን እየቀጠፈ ይገኛል፡፡ ከዚህ አንጻር አሁን ያለንበት ወቅት ከባድ አገራዊ ፈተና ያጋጠመን ጊዜ ነው፡፡መንግሥትም የዓለም ስጋት የሆነውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ለመግታት አምስት ቢሊዮን ብር መድቧል፤ 30 ሚሊዮን ተማሪዎች ትምህርት እንዲያቋርጡ ወስኗል:: በቫይረሱ የተጠቁ ዜጎችም በየጊዜው በጤና ሚኒስቴር በኩል እየተነገረ ነው፡፡ የሃይማኖት አባቶችና የእምነት ተቋማትም ለተከታዮቻቸው መልዕክት እያስላለፉ ናቸው::ሆኖም እምነትና ጥንቃቄ ጎን ለጎን መሄድ ካልቻሉ ብዙ ዋጋ ሊያስከፍሉ ይችላሉ፡፡ ወረርሽኝ በሚከሰትበት ጥንቃቄ ማድረግ እየተቻለ ፈጣሪ ያድነኛል ብሎ እጅን አጣምሮ ማየት ተገቢ አይደለም የሚሉት ኡስታዝ አህመዲን፣ ኮሮና ቫይረስን ስርጭት ለመግታት ሲባል በሃይማኖት መሪዎችና በእምነት አባቶች የሚሰጡ መልዕክቶች፣ በመንግሥት የሚተላለፉ ውሳኔዎችን፣ በጤና ባለሙያ የሚገለጹ የመከላከያ መንገዶቹን መተግበር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡የኢትዮጵያን ወንጌላውያን አቢያተክርስቲያናት ህብረት የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ መጋቢ ዘሪሁን ደጉ በበኩላቸው የኮሮና ቫይረስ ፈጣንና በቀላሉ ሊተላለፍ የሚችል መሆኑን ከጣሊያንና ከስፔን አገራት መረዳት ይቻላል ይላሉ፡፡ እነዚህ አገራት በኢኮኖሚም ሆነ በሥልጣኔ ጫፍ የረገጡ ቢሆንም በከፋ ሁኔታ በቫይረሱ የተጠቁት ሕዝባቸው መንግሥት፣ የጤና ባለሙያዎችና የሃይማኖት መሪዎች የሚያስተላልፉላቸውን መልዕክቶችና ውሳኔዎች ችላ በማለታቸው እንጂ ሃይማኖት ስለሌላቸው አይደለም ብለዋል፡፡በተለይ ጥግግትን ባለመጠበቃቸውና ራስን ሰዎች ከሚበዙበት አካባቢዎች እንዲቆጠቡ የተላለፉ መልዕክቶችን ተግባራዊ ባለማድረጋቸው ዛሬ ጣሊያን ብቻ በኮሮና ቫይረስ ከሰባት ሺህ በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ተቀጥፎል፡፡ ከ67ሺ በላይ ዜጎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል:: እኛም ከዚህ ትምህርት ወስድን በሃይማኖት መሪዎች፣ አባቶች፣ መምህራን፣ እንዲሁም በመንግሥትና በጤና ባለሙያዎች የሚተላለፉ መልዕክቶችንና ውሳኔዎችን በማክበርና በመተግበር ራስን ከኮሮና ቫይረስ መከላከል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡\nአዲስ ዘመን መጋቢት 18/2012 ጌትነት ምህረቴ", "passage_id": "f66866398da2d44136170544308d42b8" }, { "passage": "የአገራችንን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓብይ አህመድ ለመላ የኢትዮጵያ ህዝቦችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ወቅታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። የክቡር ጠቅላይ ሚኒስተሩ መልዕክት አራት ዋና ዋና ሃሳቦችንና ጥሪዎችን የያዘ ነው። እነዚህም የኮሮናን ወረርሽኝን በቁጥጥር ሥር ማዋል፣ ከፊታችን የተጋረጠውን የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ ከፍተኛ ጉዳት ሳያደርስብን በብቃት ለመሻገር፣ ሊደቀኑብን በሚችሉ እንደ ርሐብና የምግብ ምርት እጥረት የሚያስከትላቸው አደጋዎች፣ እና ከሉአላዊነት ጋር የተገናኙ ጥቃቶችን በቁርጠኝነት መመከት፣ እንዲሁም ቀጣዩን ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ነጻና ተአማኒ ለማድረግ በጋራ እንሥራ የሚል። \nእውነት ነው በዚህ ወቅት ከእነዚህ የበለጡ ዋናዋና ጉዳዮች አገራችን የሏትም። ለሁላችንም ግልጽ እንደሆነው ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ በሆነው ኮቪድ 19 የተነሳ ዓለማችን በከፍተኛ ምጥ ላይ ናት። ወረርሽኙ እንኳንስ እንደኛ ለማደግ ድክድክ በማለት ላይ ያለ ኢኮኖሚ ያላቸውን አገራት ይቅርና በኢኮኖሚ ዕድገትና ስልጣኔ አውራ የተባሉትን እንኳን ማጣፊያ ላጠረው ችግር ዳርጓቸዋል። የኮሮና ቫይረስ ካለው እጅግ ውስብስብና ፈታኝ የመስፋፋት ባህሪና በእኛ አገር ካለው አኗኗርና የህክምና መሰረተ ልማት አንጻር እጅግ ፈታኝ ነው። \nስለሆነም ያለን ብቸኛ አማራጭ ከህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ያለምንም ማወላወል መተግበር ብቻ ሆኗል። ይህን ተግባራዊ ለማድረግም መንግስት ከችግሩ ባህሪና ደረጃ በመነሳት የተለያዩ የመፍትሄ እርምጃዎችን ወስዷል። አሁንም በመውሰድ ላይ ይገኛል። በተለይም ችግሩን ከመፍታት አንጻር ዓይነተኛ መፍትሄ የሆነውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማክበርም ሆነ በማስከበር ሁላችንም እንደዜጋ የተጣለብንን ኃላፊነት መወጣት ለነገ የምንለው ሥራ ሊሆን አይገባም። \nየኮሮና ወረርሽኝ በጤና ላይ ከሚያስከትለው ጉዳት በተጨማሪ የሚያስከትለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግርም እጅግ ከባድ ነው። ለዚህም ነው ዶክተር ዓብይ አህመድ በመልዕክታቸው “በኢኮኖሚው ዘርፍ የተጋረጠብንን አደጋ በመቀነስ ወረርሽኙ በፈጠረው ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ሥጋት ምክንያት ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መቀዛቀዛቸው ምጣኔ ሀብታችን ላይ ከፍተኛ ጫና እንዳይፈጥርብን ከበፊቱ በተለየ ልዩ ልዩ ዘዴዎችን ቀይሰን በመንቀሳቀስ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ ይገባናል” ያሉት። \nከዚህ አንጻር መንግስት በኮቪድ 19 ምክንያት ኢኮኖሚው የከፋ አደጋ እንዳይገጥመው ቀደም ብሎ በመዘጋጀት የወሰደው እርምጃ ኢኮኖሚውን እንደታደገው ታይቷል። በዚህም ችግሮችን ወደ ዕድል በመቀየር በኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በአበባ፣ በቡናና በሥጋ ኤከስፖርት ላይ የታዩ ስኬቶች ለዚህ ማስረጃ ናቸው። ይሁንና ችግሩ አሁንም አልተቀረፈምና የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ለኢኮኖሚው ጤናማነት የየበኩላቸውን ሊወጡ ጊዜው አሁን ነው። \nሌላውና አንገብጋቢው ወቅታዊ ሁኔታ ከምርጫ ጋር የተያያዘው ነው። ዓለምና አገራችን ሰላም ሆነው ቢሆን እጅግ ተስፋ የተጣለበት አገራዊ ምርጫ ዘንድሮ በአገራችን ይካሄድ ነበር። ይሁንና ኮሮና የተባለ ወረርሽኝ ተከሰተና ይህ መሆን አልቻለም። ይህ የሆነው ደግሞ ከምንም ነገር ቅድሚያ የሚሰጠው የህዝብና የአገር ደህንነት በመሆኑ ነው። ህዝብ ሳይኖርና ጤናው ሳይጠበቅ ምርጫ ቀርቶ ሌላም እጅግ አስፈላጊ ነገር እንኳን ማከናወን አይቻልም። \nከዚህ አንጻር ለህዝብ ጤናና ደህንነት ታስቦ ምርጫው መራዘሙና ይሄው ሂደት ህገ መንግስታዊነትን ተከትሎ መተግበሩ ይበል የሚሰኝ ነው። ከዚህ በተቃራኒው በመሄድ ምርጫው ዘንድሮ ካልተካሄደ ሞቼ እገኛለሁ አገር ይበጠበጣል የሚሉ ኃይሎች ግን አካሄዳቸው ጤናማ አይደለምና ሰከን ብለው ሊመረምሩትና ሊስተካከሉ ይገባል። \n“በኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲ እንዲያብብና ሀገራዊ መግባባት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ገዥው ፓርቲ በቀጣይ ጊዜያት በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በውይይትና በምክክር መሥራቱን ይቀጥላል። ምንም እንኳ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የሚኖረን አመለካከት አንድ ዓይነት ባይሆንም ያለችን ሀገር ግን አንድ ናት። ለአንዲቷ ሀገራችን ስንል በሰከነ፣ በሰለጠነና ነገን አርቆ በሚያይ በሳል ስሜት ውይይትና ምክክር ማድረጋችንን አናቋርጥም” በማለትም ዶክተር ዓብይ አህመድ መንግስት ያለውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል። \nበአጠቃላይ አገራችን አሁን ካለችበት ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር ኮሮናን በብቃት በመከላከል፣ የኢኮኖሚውን ደህንነት በማረጋገጥና ድህረ ኮሮናም ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊና ነጻ ምርጫ ለማካሄድ ተገቢውን ዝግጅት ማድረግ የሁላችንም ኃላፊነት ይሆናል!\nአዲስ ዘመን ሰኔ 7/2012", "passage_id": "1623bce0cdbefea323aaef0fa7d96e92" } ]
5674f51ca4e8bb0178e5682c7af09399
1126c135988a9993dc3199738bcb5753
‹‹ተቃዋሚዎች ብቻ ሳይሆን እንደ እኔ ያሉ የፖርቲ አባል ያልሆኑ ግለሰቦች የተካተቱበት ስለሆነ አሁን ያለው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አቃፊ ነው›› – ዶክተር አሰፋ በቀለ የትግራይ ክልል መንገድና ትራንስፖርት አስተባባሪ
ክፍለዮሐንስ አንበርብር አዲስ አበባ፡- በትግራይ ክልል አሁን ያለው ጊዜያዊ አስተዳደር በጣም አቃፊና የተለያዩ የፖለቲካ አባላት በጊዜያዊ አስተዳደሩ ያሳተፈ መሆኑን የትግራይ ክልል በመንገድና ትራንስፖርት ዘርፍ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ አስተባባሪ የሆኑት ዶክተር አሰፋ በቀለ ተናገሩ::ከአማራ ክልልና የፀጥታ አካላት ጋር በመነጋገር ከመቐለ አዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት መጀመሩም ተገልጿል::የትግራይ ክልል በመንገድና ትራንስፖርት ዘርፍ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ አስተባባሪ የሆኑት ዶክተር አሰፋ በቀለ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በትግራይ ክልል አሁን ያለው ጊዜያዊ አስተዳደር በጣም አቃፊና የተለያዩ ፖለቲካዊ እሳቤ ያዙ ሰዎችን ያቀፈ ነው::በዚህም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲሁም ከፖለቲካ ፓርቲ ነጻ ሆነው ህዝብን ለማገልገል ፍላጎት ያላቸውን አካላት ጭምር በጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ውስጥ አካትተዋል:: ‹‹ቀደም ሲል የነበረው አሰራር ብዙ ጉድለት ነበረበት::አሁን ባለው አስዳደር ግን በፖለቲካ አመለካከት   ሳይገደብ ህዝብ ማገልገል ተችሏል፤” ያሉት ዶክተር አሰፋ፤ አሁን ያለው ጊዜያዊ አስተዳደር በጣም አቃፊ በመሆኑ የተለያዩ የፖለቲካ አባላት በጊዜያዊ አስተዳደር ታቅፈው እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል::“እኔን ጨምሮ የፓርቲ አባል ያልሆንን ግለሰቦች ህዝቡን በማገልገል ላይ እንገኛለን›› ብለዋል:: “ህዝብ ለማገልገል የፖለቲካ ፓርቲ የበላይ መሆን አይጠበቅም” ያሉት ዶክተር አሰፋ፤ በአሁኑ ወቅት በክልሉ በጣም የተሻለ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን እና የትግራይ ህዝብ ያጋጠመው ችግም ከየትኛው ፓርቲ በላይ መሆኑን ገልጸዋል:: በዚህ ወቅት ደግሞ ህዝብን ማገልገል ኩራት ነው ሲሉም ተናግረዋል::በዴሞክራሲ አኳያም በጣም የተሻለና አቀፊነት ስሜት ያለው እንደሆነ እና ሰዎች በአረዳዳቸው፣ የፖለቲካ ፓርቲነታቸው ሳይገለሉ በጊዜያዊ አስተዳደር መታቀፋቸው አበረታች እንደሆነ ጠቁመዋል:: እንደ ዶክተር አሰፋ ገለጻ፤ ቀደም ሲል ህዝቡ ከቤት ለመውጣት ስጋት የነበረውና ጦርነት ተመልሶ ይቀሰቀሳል በሚል እሳቤ እንቅስቃሴ ገታ ብሎ ነበር::ይሁንና የሀገር መከላከያ ሰራዊት መቐለ ከገባ በኋላ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በአግባቡ ተጀምሯል::በአሁኑ ወቅትም ታክሲዎች በተሰጣቸው የጉዞ መስርመር አገልግሎት እየሰጡ ነው::ከታሪፍ አኳያ ማጋነን እና የተሰጠውን ቦታ አለመጠቀም ይስተዋል እንደነበርና ፌዴራል ፖሊስ፣ የትራፊክ ፖሊስና የክልሉ ፖሊስ ጋር የተቀናጀ ስራ በመጀመሩ በጣም የተሻሻለ ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል:: በአሁኑ ወቅት ደግሞ በዋናነት የማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ሲሆን፤ ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላትና የፌዴራል መንግስት መዋቅር ጋር በቅርበት እየሰሩም ነው::የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በተመለከተም ከፌዴራል ትራንስፖርት ጋር በመደዋወልና መረጃ በመለዋወጥ እየተሰራ ሲሆን አስፈላጊ በሆነ ቦታ እና ሁኔታ ሁሉ ድጋፍ ለማድረግም ቃል ገብተውላቸዋል:: ከዚህ ጋር በተያያዘ ከአማራ ክልል ትራንስፖርት ቢሮ ጋር በመነጋገርም ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ ትራንስፖርት መጀመሩን የገለጹት ዶክተር አሰፋ፤ በተጨማሪም ከመቀሌ ወደ ተለያዩ የትግራይ አካባቢዎችም እንቅስቃሴ መጀመሩን አብራርተዋል:: የሀገር መከላከያ ሰራዊትም ፀጥታውን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ኃላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝም ተናግረዋል:: በአሁኑ ወቅት ከውጭ አገር ጭምር ለእርሳቸው የሚደውሉላቸው ሰዎች መኖራቸውን የገለፁት ዶክተር አሰፋ፤ የሚደውሉላቸው አብዛኞቹ ሰዎችም ጊዜያዊ አስተዳደር የሚደግፉ መሆናቸውን ነው የገለጹት::ህዝቡን ለመታደግና ወደነበረበት ሠላም ለመመለስም ዳያስፖራው ከጎናችን እንደሆኑ እየነገሩን ነው ሲሉም አስረድተዋል:: ዶክተር አሰፋ፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ሙሉ ለሙሉ ካቢኔ አቋቁሞ ሥራ ያልጀመረ ሲሆን የቀሩ ካቢኔዎች ሲሟሉ ሙሉ ለሙሉ ወደ ሥራ የሚገባ መሆኑን በመጠቆም፤ በአሁኑ ወቅት የዳያስፖራና ወጣት ምሁራን ተጋሩዎች ክልሉን መልሶ በማደራጀትና በመደገፍ ረገድ ሚናቸው የጎላ ስለሆነ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋልአዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38379
[ { "passage": "በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክኒያት በኢትዮጵያ የታወጀውና ለአምስት ወራት ያህል ተፈፃሚ ሲሆን የቆየው አስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ነሐሴ 30/2012 ዓ.ም ማብቃቱን ተከትሎ የአገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ባለፈው ሳምንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክረ ሐሳብ አቅርበው ነበር።የሕዝብ ተወካዮች ምክር አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ የቀረበው ምክረ ሐሳብ ለኮሮናቫይረስ መከላከያ ጥንቃቄዎች እየተደረጉ በዚያውም፤ “በምን መልኩ የማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ እንችላለን?” ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ ምክረ ሐሳብ መቅረቡን ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።ምክር ቤቱም ይህን ምክረ ሐሳብ ካደመጠ በኋላ፤ በሴቶች ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ እና የሕግ፣ የፍትሕ እና ዴሞክራሲ ጉዳያዮች ቋሚ ኮሚቴዎች አማካኝነት የውሳኔ ሐሳብ ማቅረባቸውን ተናግረዋል።ከእነዚህ ውሳኔዎች ውስጥ ምክር ቤት ስድስተኛ ሃገራዊ ምርጫ እንዲካሄድ ያስተለላፈው ውሳኔ፤ በ“ሕገወጥ መንግሥት እንዲተገበረ የታቀደ እና ተቀባይነት የሌለው ነው” ሲል የትግራይ ክልል መንግስት ተቃውሞውን አሰምቷል።የክልሉን መንግስት ተቃውሞ በተመለከተ የኮሙዩኒኬሽን ሃላፊ ወይዘሮ ሊያ ካሳ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግሥት ሕጋዊነቱ ከመስከረም 25 በኋላ ስለሚያበቃ ቅቡልነት ያለው ምርጫ ለማካሄድ ባለአደራ መንግስት መቋቋም አለበት ብለዋል።ከዚሁ የትግራይ ክልል መግለጫ ጋር በተያያዘ ጥያቄ የቀረበላቸው የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በፌደሬሽን ምክር ቤት የሥልጣን ዕድሜው የተራዘመለት ሕጋዊ መንግሥት እና ሕጋዊ ተቋማት ያሏት ታላቅ አገር ናት - ኢትዮጵያ ብለዋል።\n", "passage_id": "482caaf80e447b3bb670a42369064066" }, { "passage": "የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አብርሃም ተከስተ (ዶ/ር) የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሕገወጥ መንገድ የተቋቋመ ነው ላለው የትግራይ ክልል ም/ቤትና ካቢኔ የፌዴራል መንግሥት የበጀት ድጎማ እንደማያደርግ መግለጹ ክልሉን ከፌዴሬሽኑ እንዲወጣ የሚገፋ ነው አሉ።ይህ ውሳኔ እስካሁን ሲወሰድ የነበረው \"ሕገወጥ እርምጃ\" ቀጣይ አካል ነው ያሉት አብርሃም (ዶ/ር)፣ እርምጃው ኃላፊነት የጎደለው ከመሆኑ በተጨማሪ \"የትግራይ ክልልን ከፌዴሬሽኑ እንዲወጣ የሚገፋ ነው\" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀደም ብሎ የትግራይ ክልል ምክር ቤትና ከፍተኛ የሕግ አስፈፃሚው አካል በሕገመንግሥቱ ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ምንም ዓይነት ሕጋዊ ግንኙነት እንዳያደርግ የወሰነ ሲሆን፤ በማስከተልም ከፌዴራል መንግሥቱ የሚደረግ የበጀት ድጎማን እንዳያገኝ መወሰኑን የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ለብሔራዊው ቴሌቪዥን ተናግረዋል።ይህንን ውሳኔ በሚመለከት አብረሃም ተከስተ (ዶ/ር) ለቢቢሲ እንደተናገሩት ምክር ቤቱ የፌደራል መንግሥት ከክልሎች ከሚሰበስበው ገቢ ላይ ለትግራይ ክልል መንግሥት ድጎማ እንዳይሰጥ ውሳኔ ማሳለፉ \"በሌላ አገላለጽ ትግራይ የፌዴሬሽኑ አካል አይደለችም እንደ ማለት ነው\" ብለዋል።የፌዴሬሽን ምክር ቤቱን ውሳኔ \"በትግራይ ክልልና ሕዝብ ላይ ጦርነት እንደማወጅ\" አድርገው እንደሚቆጥሩት የተናገሩት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ለዚህም ደግሞ ምክንያታቸውን ሲገልፁ ፌዴሬሽኑ እና የፌዴሬሽኑ አባል መንግሥታት አንዱ የሚያገናኛቸው የበጀት ሥርዓቱ መሆኑን አመልክተዋል። የትግራይ ክልል የፌዴሬሽኑ አባል ናት ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንት አብረሃም (ዶ/ር)፤ እርምጃው ፌዴሬሽኑን የሚበትን ነው ብለዋል።የፌዴሬሽኑ አባላት አንዱ መሳሪያ የበጀት ግንኙነቱ ነው የሚሉት አብረሃም (ዶ/ር) ትግራይን ከበጀት ውጪ ማድረግ ማለት \"ከፌዴሬሽኑ እንድትወጣ የሚገፋ ነው\" ነው ሲሉ ተናግረዋል።እርምጃውን \"በጣም አደገኛ\" ያሉት አብረሃም (ዶ/ር)፣ አገሪቷን ወደ ቀውስ የሚያስገባ፣ የሚበትን በማለት \"ኃላፊነት የጎደለው እርምጃ\" ሲሉም ኮንነውታል።የፌደራል መንግሥት ገቢ የሚሰበስበው ትግራይን ጨምሮ ከክልሎች ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ይህንኑ መልሶ ለክልሎች እንደሚያከፋፍልም ተናግረዋል።ከትግራይ የሚሰበስበውን ገቢ ለትግራይ አላካፍልም ማለት \"እብደት ነው\" በማለት ውሳኔውን አጣጥለውታል።የፌዴሬሽን ምክር ቤቱ እንዳለው ወደዚህ እርምጃ የሚገባ ከሆነ ክልሉ ለፌደራል መንግሥቱ ከትግራይ የሚሰበስበው ገቢ ላይ እርምጃ እንደሚወስድም አመልክተዋል።እርምጃው ምን ዓይነት ነው ተብለው የተጠየቁት አብርሃም ተከስተ (ዶ/ር) የፌደራል መንግሥት ባለፈው ዓመት ብቻ ከትግራይ ክልል ወደ ሰባት ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን፣ በዚህ በተያዘው 2013 ዓ.ም ደግሞ ወደ ዘጠኝ ቢሊየን ብር እሰበስባለሁ ብሎ ማቀዱን ገልፀዋል።ስለዚህ ይህንን ሰብስቦ ሕጋዊ የፌዴሬሽኑ አካል ለሆነችው ትግራይ አላከፋፍልም የሚል መንግሥት \"የእብደት ሥራ ነው\" በማለት እንዲሁ ዝም ብለን አናይም ሲሉ ተናግረዋል።የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሕገወጥና ተፈጻሚነት የሌለው ነው ያለውና ባለፈው ዓመት ማብቂያ ላይ ከሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች በተለየ በትግራይ ክልል በተናጠል የተካሄደውን ምርጫ ተከትሎ የተቋቋማው የክልሉ መንግሥት ላይ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚሁ መሰረትም ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ከትግራይ ክልል ከፍተኛ አስፈፃሚ አካላት ጋር እንደሕጋዊ አካላት በመቁጠር ደብዳቤ መፃፃፍ፣ መረጃ መላላክ፣ የፌዴራል ተቋማት ለክልል ተቋማት የሚሰጧቸውን ድጋፎች መስጠት፣ በፌዴራል ደረጃ የሚካሄዱ መድረኮች ላይ ማሳተፍ የመሳሰሉ ጉዳዮችን እንዳያከናውኑ ወስኗል።ከዚህም ጎን ለጎን የክልሉ ሕዝብ መሰረታዊ የልማትና የአገልግሎት ተጠቃሚነቱ እንዳይስተጓጎል እንደ ቀበሌ ፣ወረዳ ፣ ከተማ ካሉ ሕጋዊ መዋቅሮች ጋር ብቻ ግንኙነት እንደሚደረግና በዚህም ላይ ክትትል እንደሚደረግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አደም ፋራህ ለኢቲቪ ተናግረዋል።የበጀት ድጎማን በተመለከተም \"በሕገወጥ መንገድ የተቋቋመው የትግራይ ምክር ቤትና ካቢኔ ሕጋዊ ሰውነት ስለሌለው\" ከፌዴራል መንግሥት የበጀት ድጎማ እንደማያገኝ ተነግሯል። ነገር ግን የፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ክልል ካሉ የከተማ አስተዳደሮች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ጋር በሚኖር ግንኙነት አማካይነት ሕዝቡ ማግኘት የሚገባውን መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲያገኝ የሚደረግ መሆኑና ክትትልም እንሚደረግበት ተነግሯል። ", "passage_id": "eef0117128bc3c5705d362f66e7b6d20" }, { "passage": "በኢትዮጵያ የሕግ ልዕልና ለማክበር የተጀመረው ሂደት ፖለቲካዊ መልክ ይዟል አሉ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕስ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል።ሂደቱን ትግራይን ለማንበርከክ የሚደረግ ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ይህም የውጭ እጅ አለበት በማለት በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። ", "passage_id": "e8f37305adb020308cbe4754fb603981" }, { "passage": "በኢትዮጵያ በነሐሴ 2012 ዓ.ም ሊደረግ ታስቦ የነበረው ሀገር አቀፍ ምርጫ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ምክንያት የቅድመ ምርጫ ተግባራትን ማከናወን አልቻልኩም በማለት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫው በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንደማይካሄድ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ ከዚህም በኋላ የሕገ መንግስት ትርጉም ተሰጥቶበት ምርጫው እንዲራዘም ተወስኗል፡፡\nየትግራይ ክልል ገዥ ፓርቲ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አድርጎት በነበረው ስብሰባ ብልፅግና ፓርቲ ቀድሞውኑም የ2012 ሀገር አቀፍ ምርጫን ለማከናወን ሙሉ ፈቃደኝነት አላሳየም ሲል መወንጀሉ ይታወሳል፡፡ የክልሉ ምክር ቤትም ምርጫ ኮሚሽን በማቋቋም የክልል ምክርቤት ምርጫ እንዲካሄድ ወስኗል፡፡ የትግራይ ክልል አሁን ምርጫ ካደረገ በሚቀጥለው ዓመት በሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ላይ ይሳተፋል፡፡ የኮሚሽኑን ዕጣ ፋንታና ሕጋዊነት በተመለከተና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ አል ዐይን ከትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽነር ሙሉወርቅ ኪዳነማርያም ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡\n በትግራይ ክልል አሁን ምርጫ የሚደረግ ከሆነ ከ9 እስከ 10 ወራት ባለው ጊዜ ውስጥ ደግሞ በሀገር ደረጃ ምርጫ እንደሚደረግ መንግስት ገልጿል፡፡ታዲያ በሀገር አቀፉ ምርጫ ላይ የትግራይ ክልል ይሳተፋል ወይስ አይሳተፍም?\n ውሳኔው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ነው፡፡እና ከዛ ቀደም ብሎ ምርጫ በማካሄድና ባለማካሄድ በፌዴራል መንግስትና በትግራይ ክልል መንግስት መካከል ያለመስማማቶች እንደነበሩ ይታወቃል፡፡ ይህ ሁሉም ሰው የሚውቀው ነው፡ስለዚህ በሕገ መንግስት ዙሪያ ጥያቄዎች ተነስተው ነበር፤ ጥያቄዎቹ የተፈቱበት አግባብ በትግራይ መንግስትም ሆነ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት አልነበረውም፡፡ ስለዚህ የክልሉ ምክር ቤት ይህንን የምርጫ ኮሚሽን ለማቋቋም ተገዷል፡፡ምክንያቱም በሕገ መንግስቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫዎችን የመከታተል ሥልጣን አለው፡፡የተሰጠውን ሥልጣንም ሊወጣ አልቻለም ጥያቄው ቀርቦለታል፡፡ በተገቢው መጠን ማካሄዴ አልተቻለም፡፡ ጥያቄው ቀርቦለታል፡፡ማካሄድ አትችሉም የሚል ውሳኔ ነው የሰጠው፡፡ምርጫ የማካሄድና ያለማካሄድ ፈቃጅ ሰጭ ሃይል የለም፡፡ ምርጫ የሚያካሂድ ድርጅት እንጅ ፈቃድ የሚሰጥና የሚከለክል ድርጅት አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዲሁም የትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽን ምክር ቤቱ የሰጠውን ሥልጣን ነው የሚያስፈጽመው እንጅ ምርጫ ወሳኝና አድራጊ ፈጣሪ አይደለም፡፡በመንግስት ውሳኔ መሰረት የሚሰራ አካል ነው፡፡ ስለዚህ የትግራይን ሕዝብ የመምረጥ መብት የመከልከል መብት የለውም በሚል ነው ይህንን የምርጫ ኮሚሽን ምክር ቤቱ ሊያቋቁም የተገደደው፡፡በዛ መሰረት የፌዴራሉ መንግስት ምርጫውን እንዳልወደደው ይታወቃል፡፡ ያለመውደድ ሌላ ነገር ሆኖ በሁለቱ መካከል ውይይትና ሥምምነት ቢደረግ ጥሩ ነበረ ሊደረስ ግን አልቻለም፡፡ምርጫው መካሄድ አለበት የለበትም የትግራይ ክልልና የፌዴራል ብቻ አይደለም ጥያቄው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎች የሚነሳ ነው፡፡መፍትሔው ምንድነው መሆን ያለበት የሚልም ከግራና ከቀኝ የሚቀርብ ሃሳቦች አሉ፡፡\n\n የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 102 ንዑስ አንቀጽ 1 በፌዴራልና በክልል የምርጫ ክልሎች ነፃና ትክክለኛ ምርጫ በገለልተኝነት እንዲያካሂድ ከማንኛውም ተፅዕኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል። በዚህ መሰረት ምርጫ ማድረግ የሚችል አንድ ብሔራዊ ተቋም ነው አለ የሚለው የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን ሕገ መንግስቱ ከሚለው ጋር አይጋጭም\n ሕገ መንግስቱ የአንድን ሉዓላዊ ክልል የመምረጥ መብት የማገድ ሥልጣን አለውም አይልም፡፡ ስለዚህ ያንን አግዳለሁ የሚል ከሆነ ክልሉ ያለው ምርጫ ምርጫ ማካሄድ ነው፡፡ ስለዚህ ምርጫ የሚያካሂድለት የራሱ ድርጅት ማንም አይደለም አፌክት የሚያደርገው ይሄ ክልሉን ነው አፌክት[የሚመለከተው] የሚያደርገው፡፡ የክልሉ ሕዝብ ራሱን በራሱ የማስተዳደር መብት እየተጠበቀለት ነው፤ ሕገ መንግስቱ የጠበቀለት ነው፤ይህንን ማንም መከልከል አይችልም፡፡\n ራስን በራስ ማስዳደር እንዳለ ሆኖ የክልል ምርጫ ኮሚሽን ማቋቋም ከሕገ መንግስቱ አንቀጽ 102 ጋር አይጋጭም?\n ምርጫ ቦርድ ብቻ ነው የሚል ካለ ስለዚህ እርሱ ቢፈርስስ አላደርግም ቢልስ ሀገሪቱ ትታሰራለች ማለት አይደለም፡፡ የሀገሪቱ ሕዝቦች ይታሰራሉ ማለት አይደለም፤ ማንም አፌክት የሚያደርግ አይደለም፡፡የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አካል እንጅ ፈቃጅና ከልካይ አይደለም፡፡ ምርጫ ለማድረግና ላለማድረግ ምርጫው እንዴት ተካሄደና እየተካሄደ ነው የሚል ብቻ ሆኖ ለመታዘብና ለማስፈጸም የቆመ አካል ነው፡፡ እሱ አላስፈጽምም ሲል እንግዲህ የሕዝብ የመምረጥ መብት ይቀራል ማለት አይደለም፡፡\n ፡- ኮሚሽኑ ለዚህ ምርጫ ተብሎ ብቻ የተቋቋመ ነው ወይስ በቀጣይም ይቀጥላል?\n አሁን ገለልተኛና ነጻ የሆነ ታዛቢ መኖር አለበት፡፡ አንድ ምርጫ ታአማኒ እንዲሆን የሚል ለታዛቢዎች ሲባልም አይደለም ነገር ግን በትግራይ ከጣቢያዎች ጀምሮ በህዝብ የተመረጡ ታዛቢዎች አሉ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለመወዳደር ገብተዋል፡፡ እነዚህም የራሳቸው ፍላጎት ያላቸው እና የሚወዳደሩ ናቸው፡፡ ስለዚህ ወደ ክልሉ ታዛቢዎች መምጣት ይችላሉ ወይስ አይችሉም የሚለው ጥያቄ ካለፉ ሁኔታዎች እንኳን ታዛቢዎች ኢንቨስተሮችም የተከለከሉበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ይሄ ትልቅ ጥያቄ ነው፡፡ በሁለቱ መካከል ያለው የግንኙነት ችግር ፖለቲካ የፈጠረው ነው፡፡ አሁን ግን የትግራይ ህዝብ አምስት ዓመት ስለሞላው በድል ያገኘውን መብት አሳልፎ መስጠት አይፈልግም፡፡ስለዚህ ይህንን አሳልፎ ላለመስጠት፣ ይህንን እንዲሆን ያደረገ ሕዝብ ተከልክለሃል ሊባልም አይገባውም፡፡ ይሄ ብዙ መስዋዕትነት የከፈልኩበት መብቴ ነው፡፡ ስለዚህ ሕዝቡ የደገፈው ምርጫ ነው፡፡ ስለዚህ ለማን ፍላጎት ሲባል ነው የማይካሄደው፡፡ ሕዝቡ አምስት ዓመት የሠጠው ኮንትራት አለ፡፡ ሕጋዊ መንግሰት አቋቁማለሁ የሚል ከሆነ ለዚህ ዋነኛው ነገር መንግስት የሚቋቋመው ለማንም አይደለም ለትግራይ ብቻ ነው፡፡ የትግራይ ህዝብ አልፈልግም አዲስ መንግስት ካለ የትግራይ ህዝብ ምርጫ ነው፡፡ ተገዶ አይደለም የሚያካሂደው ከጫፍ እስከ ጫፍ ሕዝቡ ራሱን በራሱ አደራጅቶ የሚያካሂደው ነው፡፡ ምርጫ ኮሚሽኑ ይህንን ምርጫ ለማከናወን ከ29ሺ በላይ አስፈጻሚዎች፣ታዛቢዎች፣ቅሬታ ሰሚዎች በየደረጃው ያሉበት ነው፡፡ ይሕንን ፖለቲካሊ ማየት ትንሽ ያስቸግራል፡፡\nታዛቢዎቹ እነማን ናቸው?\n የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይከተላቸው የነበሩትን ሕጎች በምንም አይነት ሳይዛነፉ ተግባራዊ ሆነዋል፡፡ስለዚህ ከየቀበሌው ጀምሮ የሕዝብ ታዛቢዎች ተመርጠዋል፡፡ ቅሬታ ሰሚዎች ተመርጠዋል ከጣቢያዎች ጀምሮ፡፡\n አሁን በትግራይ ምርጫ የሚደረግ ከሆነ በቀጣይ ዓመት ደግሞ በሀገር ደረጃ ምርጫ ይደረጋል ተብሏል፡፡ ስለዚህ ሀገር አቀፍ ምርጫው ሲደረግ በፌዴራል ደረጃ ትግራይን የሚወክሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምርጫስ እንደት ይሆናል? ከዚህ በኋላስ እንዴት ነው በሀገሪቱ ተመሳሳይ የምርጫ ሰሌዳ የሚኖረው አሁን በትግራይ ምርጫ ከተደረገ?\n ይሄ የሚመለከተው ትግራይን ብቻ ነው፡፡ በትግራይና በፌዴራል መንግስታት መካከል የፖለቲካ ድርድር ፣ስምምነትና ሰላም ሲመለስ ሥርዓቱ እንደዚህ ሆኖ ይቀጥላል ተብሎ ዲፋይን ሲያደርግ የሚሆኑ ሁኔታዎች ናቸው ማለት ነው በዚህ ነው ሊመለስ የሚችለው፡፡\n ስለዚህ ምርጫ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲደረግ ለፓርላማ ተመራጮች ሲባል ድጋሚ ይደረጋል ?\nድጋሚ ማድረግ አይጠበቅም፡፡ ይህ ምርጫ የሚመለከተው ትግራይን ብቻ ነው፡፡ በፌዴራል የትግራይ ውክልና ሲፈለግ ሌላ ጉዳይ ይሆናል፡፡ በፌዴራል ደረጃ የሚወከሉ ሰዎች ምርጫ ይደረጋል ማለት ነው፡፡ ትግራይን በፌዴራል የሚወክሉ ሰዎችን ለመምረጥ ምርጫ ይካሄዳል ማለት ነው፡፡ ፌዴራል ለሆነው ጉዳይ ፌዴራሉ ይቋቋማል፣የፌዴራል መንግስት ሊቋቋም የሚችለው ከፓርላመንታዊ ዴሞክራሲ ስለሆነ ከፓርላማ የሚወጣ መንግስት ይኖረናል፡፡ ወደ ፓርላማ የሚሄዱ ሰዎች ይመረጣሉ ማለት ነው፡፡ በሹመት ስለማይሆን ትግራይ ያለ ፓርቲዎችም ተፎካክረው ምርጫ ተደርጎ ነው ወደ ፓርላማ የሚላኩት፡፡\n በሕገ መንግስቱ መሰረት የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን ሕጋዊ አይደለም የሚሉ አሉ፣ ምክንያቱም በብሔራዊ ደረጃ አንድ የምርጫ ቦርድ እንደሚኖር ስለሚደነግግ፤ስለዚህ እርስዎ የሚመሩት ኮሚሽን ሕጋዊ የሚሆነው በምን የሕግ አግባብ ነው?\nሕጋዊ ነን፡፡ እንግዲህ የትግራይ ክልል ምክር ቤት ያቋቋመው ነው ሕጋዊ ነው፡፡ የትግራይን የራስ ዕድል በራስ የመወሰን መብት እስከተቀበልክ ድረስ የትግራይ[ክልል] የወሰነውን መቀበል አለብህ፤ ትግራይን በሚመለከት ማለት ነው፡፡ ትግራይ አብሮ ወሰነው እንደ ሀገር ያካሂድልኛል ብሎ የመረጠው ወይም አሜን ብሎ የተቀበለው የምርጫ ቦርድ አላስተናግድህም ሲለው ምርጫው ምንድነው መሆን ያለበት?\n ሕጋዊ የሚዲርጉትን የሕግ አንቀጾች ሊጠቅሱልኝ ይችላሉ?\n እንግዲህ ሕጋዊ ብለን እየሰራን ነው፡፡ ስለወደፊቱ በፖለቲካ ሃይሎች መካከል በሚኖር ድርድር ሊፈቱ የሚችሉ ናቸው፡፡ዝም ብሎ ይሄ ነገር በሃይል ይፈታል ምናምን የሚል ነገር አይደለም ያለው፡፡እኔ ሰላም እንዲኖር የምፈልግ ስለሆንኩኘ ማለት ነው፡፡\n ታዲያ ኮሚሽኑን ሕገ መንግስቱ ይደግፈዋል ማለት ነው?\n አታካሂዱም ሲል እሽ እሱ ብሎናል፤ እኛ ታዲያ ምን እናድርግ?\n ምርጫ የሚደረግ ከሆነ ለምርጫው የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች ተሟልተዋል ወይስ ገና ናቸው?\n የሎጀስቲክ ዝግጅታችን ጥሩ ላይ ነው ያለው፡፡ በወቅቱ እንደርሳለን፡፡ ብዙ ነገሮች ማከናወን ችለናል፡፡ በመርሃ ግብራችን መሰረት እየሄድን ነው፡፡\n ምርጫውን መቼ ለማድረግ ነው ያቀዳችሁት?\n ሰሞኑን ዝርዝር መርሃ ግብሩን እናወጣለን፡፡ እና ምርጫ 2012 ነው እንደገባኝ ስለዚህ 2012 መደረግ አለበት፡፡ መስከረም አካባቢ ሊካሄድ ይችላል መስከረም መጀመሪያ ላይ ሊሆን ይችላል፡፡ ከፓርቲዎችም ጋር ውይይት ተደርጎ ይወሰናል፡፡\nመሰረታቸውን ትግራይ ክልል ላይ ያደረጉ ነገር ግን በምርጫው የማይሳተፉ ፓርቲዎች አሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ ምርጫው ዴሞክራሲያዊ ይሆናል፡፡\nስለማይመለከታቸው ነው እንጅ ከመሃል መሳተፍ የሚፈልጉ ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ የፖለቲካ ልዩነቱ የፈጠረው ይመስለኛል፡፡ ምርጫው መካሄድ የለበትም ያሉት አይሳተፉም፡፡ መካሄድ አለበት የሚሉት ይሳተፋሉ፡፡\n ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምንም እንኳን ከዚህ በፊት ቅሬታዎች ሲነሱበት የነበረ ቢሆንም ምርጫዎችን በማድረግ ልምድ አለውና በዚህ ልታካሂዱ ባሰባችሁት ምርጫ ቦርዱን ታነጋግሩታላችሁ፤ ግንኙነታችሁ ምን ይመስላል?\n ምንም የሚያገናኘን ነገር የለም፡፡ የእኛ ኮሚሽን ለክልል ምክር ቤት ነው ተጠሪነቱ፡፡ ክልሉን በሚመለከት የክልል ምክር ቤት አለቃ የለውም፡፡ ልምድን በሚመለከት ልምድ ያላቸው ሰዎቹ ናቸው ተቋሙ ነው የሚለውን ማየት ነው፡፡ ምርጫ ያደረጉትም እኮ እዚህ ትግራይ ውስጥም አሉ፡፡\n የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወልቃይትና ራያ እልባት ሳይሰጣቸው ወይም የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ኮሚሽን ውሳኔ ሳይሰጥ በአካባቢዎቹ ምርጫ መደረግ የለበትም የሚሉ ፓርቲዎችና ቡድኖች አሉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ምላሽ አለዎት?\n የትግራይ ክልል ምርጫ መደረግ አለበት ብሏል፡፡ የት ለሚለው ትግራይ ውስጥ ፡፡ስለዚህ ትግራይ ውስጥ ምርጫ ይደረጋል፡፡ የክልሉ መንግስት ምርጫውን ያካሂዳል በክልሉ ውስጥ ክልሉ ውስጥ ጥያቄ አለኝ የሚል አካል ካለ ይሄ ሌላ ጉዳይ ነው፡፡\nአሕገ መንግስት ተጣሰ በሚል የፌዴራል መንግስትም የትግራይ ክልል መንግስትም እርስ በእርስ የቃላት ምልልሶች ውስጥ ገብተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት መሰረት በፌዴራልና በክልል የምርጫ ክልሎች ነፃና ትክክለኛ ምርጫ በገለልተኝነት እንዲያካሂድ ከማንኛውም ተፅዕኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል የሚል ድንጋጌ አለ፡፡ በዚህ መሰረት የዚህ ተቋም ኃላፊ ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ናቸው፡፡ እርሶዎ ደግሞ በኢትዮጵያ ውስጥ በተቋቋመ ሌላ ኮሚሽን ( ከሕገ መንግስቱ አንቀጽ 102 ንዑስ አንቀጽ 1 ውጭ) ኃላፊ ነዎት፡፡ በዚህም መሰረት ታዲያ ማነው ሕጋዊ ኃላፊ ማነው ሕገ ወጥ ኃላፊ?\n ትግራይ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን ሥልጣኑ የራሱ ነው፡፡ እኔ ከሰዎች ጋር ምንም ጥላቻም  የተለየ አመለካከት የለኝም ፡፡የተሰጠኝ ስራ ይህንን እንድፈጽም ነው፡፡ ይህንን ሥራ የማስፈጽምበት መዋቅር ተፈጥሮልኛል፡፡ ስለዚህ ሕጋዊ ተቋም ነው፤ የምመራው መንግስት ያቋቋመው ነው፡፡ የክልሉ ምክር ቤት ያቋቋመው ተቋማ ሕጋዊ አይደለም ሊባል አይችልም፡፡ስለወ/ሪት ብርቱካን ምን እንደሚያደርጉ ቢናገሩ ይሻላል፡፡ሥልጣኔን ቀምቶኛል የሚሉ ከሆነ እኔ አይደለሁም ማለት ነው፡፡\n ትግራይ ውስጥ እኮ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቅርንጫፍ አለ፡፡ ነገር ግን ክልሉም ሌላ አቋቋመ፡፡ ይህ እንዴት ይቻላል ሕግን አይጻረርም?\n እኔ እንጃ በፊት ነበረ፤ እሱ አልሰራ ካለ ሌላ ይፈጠራል፡፡\n", "passage_id": "d4152d34c4ce39178a85eb2fb057e90a" }, { "passage": "የትግራይ ክልል ከሌላው ኢትዮጵያ ተለይቶ ያካሄደውን ምርጫ ያሸነፈው ህወሓት በዛሬው ዕለት በክልሉ አዲስ መንግሥት መስርቷል። በዚህ ምስረታ የክልሉ አዲስ ምክርቤት ሥራ የጀመረ ሲሆን የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት ሆነው የተሾሙትዶ/ር ደብረጺዮን ገ/ሚካኤልም ቃለ መሓላ ፈፅመዋል።የኢትዮጵያ የፌዴራል ሥርዓት እንደ አዲስ የሚስተካልበት ግዜ ደርሷል ሲሉ ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።።\n", "passage_id": "8428e4ea52236c62880b90a9e7a4e987" } ]
ee40f0e448763b77713e7a89cb07f901
e7584ff8435369f353abb110b2d103a6
በከተማው የክለቦች ቻምፒዮና ክብረወሰን ተሻሻለ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት የሚካሄደው ዓመታዊው ፔፕሲ የአዲስ አበባ ክለቦች አትሌቲክስ ቻምፒዮና ለ37ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም በመካሄድ ላይ ይገኛል።ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን የያዘው ውድድሩ በተለያዩ ርቀቶች የሩጫና ሜዳ ተግባራት አትሌቶችን በማፎካከር በርካታ ክብረወሰኖች እየተሻሻሉበት ይገኛል። በውድድሩ ሁለተኛ ቀን ውሎ ትናንት በተካሄደው የሴቶች አንደኛ ዲቪዚዮን አስር ሺ ሜትር ውድድር ክብረወሰን ተሰብሯል።በኢትዮጵያ ቻምፒዮና በአትሌት ለተሰንበት ግደይ 32፡10፡90 ተይዞ የነበረው የርቀቱ የኢትዮጵያ ክብረወሰን ዘንድሮ በአትሌት ዘይነባ ይመር በስድስት ሰከንድ ሊሻሻል ችሏል። በቻምፒዮናው ላይ በአንደኛ ዲቪዚዮን ከታቀፉ አምስት ክለቦች የተሳተፉ ሲሆን በሁለተኛ ዲቪዚዮን ከታቀፉ ሃያ ክለቦች የተውጣጡ በአጠቃላይ አንድ ሺ አትሌቶች ተሳታፊ ሆነዋል።ውድድሩ ክለቦች የአትሌቶቻቸውን አቅም ከመለካት ባሻገር በሃገር አቀፉ የአትሌቲክስ ቻምፒዮና ተሳታፊ ለመሆን የሚያስችላቸውን ምዘና የሚያደርጉበት እንዲሁም ስልጠናቸውን በመገምገም ራሳቸውን የሚያጎለብቱበት መድረክም መሆኑ ተነግሯል። ትናንት በተካሄደው የሁለተኛ ቀን ውሎ የተለያዩ የማጣሪያ እና የፍጻሜ ውድድሮች ተካሂደዋል።በሁለተኛ ዲቪዚዮን የ100 ሜትር ሩጫ በሁለቱም ፆታ የፍፃሜ ውድድሮች የተከናወነ ሲሆን፤ በሴቶች ትዝታ ደጋ ከአራዳ ክፍለ ከተማ እንዲሁም ሜሮን ተመስገን እና ፍቅርተ ሽፈራው ከዳሎል ክለብ ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል።በወንዶች በኩል ኤርሚያስ ሻጠው ከኮልፌ ቀራኔዮ ክፍለ ከተማ አንደኛ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያውን ወስዷል።የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲው አትሌት ሲሳይ አየሁ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ክለብ አትሌቱ ዘገየ ለገሰ ደግሞ ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል።በተመሳሳይ በ10ሺ ሜትር በወንዶችና ሴቶች ውድድር ፍጻሜያቸውን ሲያገኙ፤ በ1ሺ500 ሜትር፣ በአሎሎ ውርወራ እና በከፍታ ዝላይ አሸናፊ የሆኑ አትሌቶች የሜዳሊያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ነገ ቀጥሎ በሚውለው ቻምፒዮና የተለያዩ የፍጻሜ ግማሽ ፍጻሜና የማጣሪያ ውድድሮች የሚካሄዱም ይሆናል።በ5ኪሎ ሜትር በሴቶች እንዲሁም በ10ኪሎ ሜትር የወንዶች እርምጃ ውድድሮች ፍጻሜያቸውን ከሚያገኙት መካከል ይጠቀሳል።በሁለተኛ ዲቪዚዮን የሱሉዝ ዝላይ በሴቶች የማጣሪያ፣ በዲስከስ ውርወራ ወንዶች ግማሽ ፍጻሜ፣ በሁለቱም ጾታ የ400 ሜትር ፍጻሜ፣ 5ሺ ሜትር ሴት ግማሽ ፍጻሜ፣ 100ሜትር መሰናክል የሴቶች ግማሽ ፍጻሜ እና በ110ሜትር መሰናክል ሴት ግማሽ ፍጻሜ ይከናወናሉ።በአንደኛ ዲቪዚዮን ደግሞ በ100 ሜትር ሴትና ወንድ ግማሽ ፍጽሜ እንዲሁም በ110 ሜትር መሰናክል የወንዶች ግማሽ ፍጻሜ ውድድሮች በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሰረት ይካሄዳሉ። ይህ ዓመታዊ ቻምፒዮና በ1975 ዓ.ም መካሄድ የጀመረ ሲሆን፤ በፌዴሬሽኑ የተመዘገቡ ብዛት ያላቸው ክለቦች ሲሳተፉበት መቆየታቸውን መረጃዎች ያሳያሉ።ከ1991ዓ.ም ጀምሮም ፌዴሬሽኑ አቅሙን በማጎልበት ከሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ጋር በመተባበር ውድድሩ ለዓመታት በቋሚነት በመካሄድ ላይ ይገኛል። ፍጻሜያቸውን ባያገኙ ውድድሮች በቀዳሚነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የወርቅ፣ ብርና ነሃስ ሜዳሊያ የሚበረከትላቸው ይሆናል።ውድድሩ ከትናንት በስቲያ የተጀመረ ሲሆን በመጪው እሁድ 22/2012 ዓ.ም የሚጠናቀቅም ይሆናል። አዲስ ዘመን ረቡዕ የካቲት 18/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27938
[ { "passage": " እየተጋመሰ የሚገኘው የሚያዝያ ወር በዓለም ላይ በርካታ የጎዳናና የማራቶን ውድድሮች የሚስተናገዱበት ነው። ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ በሰጣቸው የተለያዩ ውድድሮች ከፍተኛ ድል በማስመዝገብ ገፍተውበታል። ባሳለፍነው ሳምንት እንኳን ፓሪስና ቦስተን ማራቶኖች ላይ አስደናቂ ድሎችን በማስመዝገብ የረጅም ርቀት ኮከብነታቸውን ለዓለም ማሳየት ችለዋል። ዛሬና ነገ በሚካሄዱ የማራቶንና የግማሽ ማራቶን ዓለም አቀፍ ውድድሮችም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከወዲሁ ለድል ታጭተዋል። የወርቅ ደረጃ የተሰጠው ዶንግዪንግ ዓለም አቀፍ ማራቶን ዛሬ ሲካሄድ በሁለቱም ፆታ የቦታው ክብረወሰን ይሻሻላል ተብሎ ይጠበቃል። በውድድሩ በተለይም በሴቶች ከዚህ ቀደም አሸናፊ የነበረችው ዋጋነሽ መካሻ ዳግም ለአሸናፊነት መታጨቷን አዘጋጆቹን ጠቅሶ አይ.ኤኤ.ኤፍ በድረ ገፁ አስነብቧል።ባለፈው ጥር ወር በዱባይ ማራቶን አራተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ 2:22:45 የሆነ የግል ምርጥ ሰዓቷን በማራቶን ያስመዘገበችው ዋጋነሽ በርቀቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተስፋ ከሚጣልባቸው ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አንዷ ነች። የመጀመሪያ የማራቶን ውድድሯን እአአ 2014 ሲንጋፖር ላይ ካደረገች ወዲህ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየች የምትገኘው የ27 ዓመቷ አትሌት፣ ባለፈው ዓመት በቻይና ሄንግሹ ያሸነፈችበትን ውድድር ጨምሮ በአራት ውድድሮች የተሻለ ሰዓት እያስመዘገበች መምጣቷ በዛሬው ውድድር ከአሸናፊነት ባለፈ ክብረወሰን ለማሻሻል አቅም እንዳላት እምነት ተጥሎባታል። ባለፈው ዓመት በለተብርሃን ሃይላይ የተመዘገበው 2:24:45የውድድሩ ክብረወሰን ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ከኬንያውያን ተፎካካሪዎቿ ጋር ልታሻሽለው ትችላለች ተብሎ ይጠበቃል።ለዚህም በውድድሩ የመጀመሪያውን ፈጣን ሰዓት የያዘችው ኬንያዊት ካሮሊን ቼፕታኑይ ያላት ጥንካሬ ፈጣን ሰዓት ሊመዘገብ እንደሚችል ማሳያ ተደርጓል። ይህች አትሌት 2:22:34 የሆነ ግል ፈጣን ሰዓት በርቀቱ ማስመዝገብ የቻለች ሲሆን፣ እአአ 2013 በፍራንክፈርት ማራቶን ባሸነፈችበት ውድድር ነበር ሰዓቱን ያስመዘገበችው። የ38 ዓመቷ ኬንያዊት እአአ 2016 የዴጉ ማራቶንን 2:27:39 በሆነ ሰዓት ካሸነፈች ወዲህ ባደረገቻቸው ውድድሮች ርቀቱን ከ2፡30 በታች ማጠናቀቅ አልቻለችም። ባለፈው ዓመትም በዚሁ ዶንግዪንግ ማራቶን አምስተኛ ሆና ስትፈፅም ማስመዝገብ የቻለችው ሰዓት 2፡34፡39 ነው።ይህም የአሸናፊነቱ ግምት ወደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት እንዲያደላ አድርጓል። ከዚህ ውድድር ክብረወሰን የተሻለ የራሷ ፈጣን ሰዓት ያላት ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አፈራ ጎደፋይ ለአሸናፊነት ከታጩ አትሌቶች መካከል ተካታለች። የ27 ዓመቷ አትሌት ባለፈው ዓመት በሻንጋይ ማራቶን አራተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ቀድሞ በርቀቱ የነበራትን ፈጣን ሰዓት ከአምስት ደቂቃ ባላነሰ በማሻሻል\n2:23:54 ማስመዝገቧ ይታወሳል። በዚሁ ውድድር በወንዶች መካከል የሚኖረው ፉክክር በኢትዮጵያዊው ግርማይ ብርሃኑ አሸናፊነት እንደሚደመደም ይጠበቃል። እአአ 2014 ዱባይ ማራቶን ላይ ሦስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡05፡49 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያስመዘገበው የ32 ዓመቱ ግርማይ የዴጉ ማራቶንን ባሸነፈበት ውድድር ተቀራራቢ የሆነ 2፡07፡26 ሰዓት አስመዝግቧል። የቀድሞው የራባት ማራቶን ሻምፒዮን ፍቃዱ ከበደም ባለፈው የዱባይ ማራቶን የራሱን ምርጥ ሰዓት በሰባ ሰከንድ አሻሽሎ\n2:08:27 ማጠናቀቁን ተከትሎ ለአሸናፊነት ይጠበቃል።በዚሁ በቻይና የወርቅ ደረጃ ተሰጥቶት ነገ በሚካሄደው ያንግዞ ዓለም አቀፍ ማራቶን የቀድሞ የውድድሩ ሻምፒዮን የሆነች ኢትዮጵያዊቷ ሱቱሜ አሰፋ የአሸናፊነት ግምት አግኝታለች።\n2017 ላይ የዚህ ውድድር አሸናፊ የነበረችው የ24 ዓመቷ ሱቱሜ ከሁለት ዓመት በፊት ለድል ስትበቃ 1፡10፡30 በሆነ ሰዓት አጠናቃለች። ባለፈው የሚላን ግማሽ ማራቶን ውድድር የራሷን ምርጥ ሰዓት ወደ 1፡07፡54 ማሻሻሏ ይታወሳል። በዚህ ውድድር ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ደጊቱ አዝመራው ቀላል ግምት የሚሰጣት አትሌት አይደለችም። የ20 ዓመቷ ደጊቱ በዚህ ዓመት ገና በመጀመሪያዋ የግማሽ ማራቶን ውድድር\n1:06:47 ሰዓት በማስመዝገብ ጥንካሬዋን ማሳየት ችላለች። ከሁለት ወራት በፊትም በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የራክ ግማሽ ማራቶን ውድድር አራተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ሰዓቷን ወደ1:06:07 አሻሽላለች። የዚህ ውድድር የአራት ጊዜ አሸናፊው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሞስነት ገረመው በሌለበት የዘንድሮው ውድድር ትውልደ ኬንያዊው የባህሬን አትሌት አብረሃም ቺሮበን የአሸናፊነት ግምት ወስዷል። ቺሮበን በነገው ውድድር እአአ 2015 በሞስነት ገረመው 59፡52 ሰዓት ተይዞ የቆየውን የቦታውን ክብረወሰን ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል። ቺሮበን ባለፈው ዓመት በውድድሩ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁም አይዘነጋም።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 12/2011 ", "passage_id": "5c796f4cfdda948382c981eb2d1363d0" }, { "passage": "በ1ሺኽ 5 መቶ የዓለም ሻምፒዮኗ ገንዘቤ ዲባባ በዓለም አቀፉ የ ቪልላ ድ ማድሪድ አንድ ሺኽ ሜትር ሩጫ ውድድር የግልዋን ፈጣን ጊዜ አስመዝግባ አሸነፈች።በቶክዮ ማራቶን ደግሞ የኬንያ አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ድል ተቀዳጁ።በእግር ኳስ የሃገር ውስጥ እና የውጭ ፕሪምየር ሊግ ዜናዎች ተጠናቅሯል፡፡ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡ ", "passage_id": "33e1404f53372ac490ea59920b86b806" }, { "passage": "አስረኛው ዙር የ2019 የዳይመንድ ሊግ ውድድር በሳምንቱ መጨረሻ በእንግሊዝ ለንደን በተለያዩ ርቀቶች ሲካሄድ ኢትዮጵያዊው አትሌት ሐጎስ ገብረሕይወት በአምስት ሺህ ሜትር ውድድር አሸናፊ ሆኗል። አትሌት ሐጎስ ገብረሕይወት የአምስት ሺህ ሜትር ውድድሩን በቀዳሚነት ያጠናቀቀበት ሰዓትም 13 ደቂቃ ከ1 ሴኮንድ ከ86 ማይክሮ ሴኮንድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ አትሌት ሐጎስ በውድድሩ ከኖርዌያዊው አትሌት ጃኮብ ኢንብሪግስተን ብርቱ ፉክክር የገጠመው ሲሆን፣ በውድድሩ የመጨረሻ 250 ሜትሮች ላይ ፍጥነቱን በመጨመር ቀዳሚ ሊሆን መቻሉም ታውቃል፡፡ ሃጎስን ተከትሎ ኖርዌያዊው አትሌት ጃኮብ ኢንብሪግስተን 13 ደቂቃ ከ1 ሴኮንድ ከ86 ማይክሮ ሴኮንድ በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ደረጃን ሲገባ ኬኒያዊው አትሌት ኒኮላስ ክሚሊ 13 ደቂቃ ከ5 ሴኮንድ ከ45 ማይክሮ ሴኮንድ ሦስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡ አትሌት ሃጎስ ከሁለት ሳምንት በፊት በሲውዘርላንድ በተካሄደው የአምስት ሺ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር 4ሺ 600 ሜትሮችን እንደሮጠ የመጨረሻ መስመር የደረሰ መስሎት በድል አድራጊነት እጁን እያነሳ ሲጨፍር ተቀድሞ አስረኛ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ በሴቶች መካከል የተካሄደው የአምስት ሺ ሜትር ውድድር የኬንያውያን የበላይነት ታይቶበታል፡፡ ሄለን ኦኒሪ 14 ደቂቃ ከ20 ሴኮንድ ከ36 ማይክሮ ሴኮንድ በሆነ ሰዓት ቀዳሚ ሆናለች፡፡ አግኒስ ጂብት 14 ደቂቃ ከ20 ሴኮንድ ከ68 ማይክሮ ሴኮንድ ሁለተኛ ስትሆን ኢትዮጵያዊቷና ለኔዘርላድስ የምትሮጠው ሲፋን ሃሰን በሦስተኛነት ውድድሩን አጠናቃለች። አትሌቷ ውድድሩን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ሰዓትም 14 ደቂቃ ከ22ሴኮንድ ከ12 ማይክሮ ሴኮንድ ሆኖ ተመዝገቧልአትሌት ሐጎስ በዳይመንድ ሊግ ወድድር አሸናፊ ሆነ ኢትዮጰያዊዋ አትሌት ለተሰንበት ግደይ አስረኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች። በአፍሪካ፣ አውሮፓ፣ እስያና ሰሜን አሜሪካ በሚገኙ 14 ከተሞች የሚካሄደው የ2019 የዳይመንድ ሊግ ውድድር ለአስራ አንደኛ ጊዜ በነሐሴ ወር አጋማሸ በእንግሊዝ በርሚንገሃም ከተማ ይካሄዳል። ውድድሩ በቀጣዩ ጳጉሜን መጀመሪያ በቤልጂየም መዲና ብራሰልስ ላይ ይጠናቀቃል፡፡የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የዘንድሮው የዳይመንድ ሊግ ውድድር በአጠቃላይ የስምንት ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ሽልማት ማዘጋጀቱ ይታወሳል። በሁለቱም ጾታዎች በተመሳሳይ በ16 የተለያዩ የውድድር አይነቶች በእያንዳንዱ ርቀት የአጠቃላይ አሸናፊ የሚሆኑ አትሌቶች የ50 ሺህ ዶላር እና የዳይመንድ ሽልማት ያገኛል። ከዚህም በተጓዳኝ በእያንዳንዱ የዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይ የ100 ሺህ ዶላር ሽልማትም የተዘጋጀ ሲሆን በተጨማሪም በእያንዳንዱ ርቀት አሸናፊ የሚሆኑ አትሌቶች ከመስከረም 17 እስከ መስከረም 26 ቀን 2012 ዓ.ም በኳታር መዲና ዶሃ ለሚካሄደው 17ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ያለማጣሪያ የሚያልፉ ይሆናል።አዲስ ዘመን  ሐምሌ 16/2011", "passage_id": "19d42af9c79a7cd0f587a953ce23d4ac" }, { "passage": "ኡጋንዳዲው ጆሹዋ ቼፕቴጌ በፈረንሳይ ሞናኮ በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ለ16 ዓመታት በቀነኒሳ በቀለ ተይዞ የነበረውን የ5000 ሜትር ሩጫ ክብረ ወሰን በሁለት ሰከንድ ማሻሻል ችሏል።የ23 ዓመቱ ወጣት ባላፈው ዓመት በዶሃ የዓለም ሻምፒዮና ላይ የ10 ሺህ ሜትር አሸናፊ በሆነበት ወቅት የ5 ሺህ ሜትር ክብረ ወሰንን ለማሻሻል እቅድ እንዳለው ገልጾ የነበረ ሲሆን በቅርብ ዓመታት ያሳካዋል ተብሎ ግን አልተገመተም ነበር።ነገር ግን በትላንቱ የሞናኮው ውድድር ላይ 5 ሺህ ሜትሩን 12 ደቂቃ 35.36 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ ቀነኒሳን ክብረ ወሰን መስበር ችሏል።ቀነኒሳ በቀለ የዛሬ 16 ዓመት ክብረ ወሰኑን ሲያስመዘግብ ውድድሩን የጨረሰው በ12 ደቂቃ 37 ሰከንድ ከ35 ማይክሮ ሰከንድ ነበር።በሚያስገርም ሁኔታ ቼፕቴጌ በዚህ ዓመት ክብረ ወሰን ሲሰብር ይሄ ሁለተኛው ነው። ባለፈው የካቲት ወር ላይ ደግሞ በተካሄደ የ5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ሰዓት ማሻሻል እንደቻለ ተነግሯል። ''ሞናኮ በጣም ልዩ ቦታ ናት፤ የዓለም ክብረ ወሰኖችን ልሰብርባት የምችልባት ከተማ ናት'' ሲል በደስታ ተውጦ ቼፕቴጌ ተናግሯል።''በዚህ ዓመት በእውነቱ ሞራልን ሰብሰብ አድርጎ ለመስራት ትንሽ ይከብዳል፤ ምክንያቱም በወረርሽኙ ምክንያት ሰዎች ከቤታቸው አይወጡም፤ ብዙ ነገሮችም በፊት እንደነበሩት አይደሉም፤ ተቀይረዋል። ነገር ግን በዚህ ሁኔታ ውስጥ በማሸነፌ በጣም ደስተኛ ነኝ።''በሌሎች ውድድሮች የዓለም ሻምፒዮኑ ኖዋህ ሊይስ የ200 ሜትር ውድድሩን በ19 ሰከንድ ከ72 ማይክሮሰከንድ በሆነ ሰዓት በማሸነፍ አይበገሬነቱን አሳይቷል። ታናሽ ወንድሙ ጆሴፈስ ደግሞ በመጀመሪያው የዳይመንድ ሊግ ተሳትፎው እሱን ተከትሎ ሁለተኛ ሆኖ መጨረስ ችሏል።ኖርዌያዊው ዓለም ሻምፒዮን ካርስተን ዋርሆልም ደግሞ በ400 ሜትር መሰናክል ውድድር በአውሮፓውያኑ 1992 በኬቨን ያንግ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን መስበር ችሏል።ለብቻው ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ሲሮጥ የነበረው ካርስተን ውድድሩን በ47 ሰከንድ ከ10 ማይክሮ ሰከንድ ጨርሷል።ኬንያዊቷ ሄለን ኦቢሪ ደግሞ የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድሩን በበላይነት ስታጠናቅቅ ሲፋን ሀሰን ደግሞ ጥቂት ዙሮች ሲቀሩት ውድድሩን አቋርጣ ወጥታለች። 5 ሺህ ብቻ ሰዎች እንዲመለከቱት በተፈቀደው የሞናኮው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይ ተመልካቾች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ ግዴታቸው ሲሆን አካላዊ ርቀትም መጠበቅ ነበረባቸው።", "passage_id": "e26d90f548d9640150005c4e6d42bca4" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ክለቦች አጭር፣ መካከለኛ፣ እርምጃና የሜዳ ተግባራት ዓመታዊ ሻምፒዮና በመከላከያ ክለብ አጠቃላይ አሸናፊነት ተጠና ቀቀ። የመከላከያ ክለብ በሁለቱም ፆታዎች እና ለአጠቃላይ አሸናፊነት የተዘጋጁትን ሦስቱንም ዋንጫዎች ወስዷል፡፡በአዲስ አበባ ስታዲየም ለተከታታይ ስድስት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ከትናንት በስቲያ ፍጻሜውን ባገኘው በዚህ ሻምፒዮና ማጠናቀቂያ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ላይ ኮሎኔል አትሌት ደራርቱ ቱሉ በመገኘት ለአሸናፊዎች የሜዳልያና የዋንጫ ሽልማት ሰጥታለች። ከፌዴሬሽኑ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት መካከልም ዶ/ር በዛብህ ወልዴ፣ አቶ ፈሪድ መሃመድ እንዲሁም የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።በዚህ ዓመታዊ ሻምፒዮና መከላከያ በሴቶች 152 ነጥብ 5 ማስቆጠር የቻለ ሲሆን፣ በወንዶች በተመሳሳይ 165 ነጥብ 5 በማስቆጠር በሁለቱም ጾታዎች የዋንጫ ተሸላሚ መሆን ችሏል።መከላከያን በመከተል ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው ሲዳማ ቡና ሆኗል። ሲዳማ ቡና በሴቶች 134 ነጥብ ሲያስመዘግብ በወንዶች ደግሞ 128 ነጥብ በመሰብሰብ ውድድሩን አጠናቋል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሻምፒዮናው ጥሩ ግምት ከተሰጣቸው ክለቦች አንዱ የነበረ ሲሆን፣ ውድድሩን ግን ያጠናቀቀው ሦስተኛ ደረጃ በመያዝ ነው፡፡ ንግድ ባንክ በሴቶች 107 ነጥብ የሰበሰበ ሲሆን በወንዶች ደግሞ 74 ነጥብ በመሰብሰብ በደረጃ ሰንጠረዥ ውስጥ መካተት ችሏል።\nበሻምፒዮናው በሁለቱም ጾታዎች የተመዘገበው አጠቃላይ ድምር ውጤት ታይቶም የአሸናፊዎች አሸናፊው ተለይቷል። በዚህም መከላከያ በ318 አንደኛ በመሆን የዘንድሮውን ውድድር ሻምፒዮና በመሆን አጠናቋል። ክለቡ ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ሻምፒዮና የነበረ ሲሆን፤ በ459 አንደኛ በመውጣት የዋንጫ አሸናፊ ነበር። በዘንድሮው የውድድር ዓመትም ተመሳሳይ የድል ባለቤት በመሆን ማጠናቀቅ ችሏል። ክለቡ አጭር፣ መካከለኛ፣ እርምጃና የሜዳ ተግባራት እያስመዘገበ ያለው ውጤት ለዘርፉ የሰጠውን ልዩ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን በሚገባ ያስመሰከረ ተብሎለታል።በዓመታዊ ሻምፒዮናው በነጥብ ድምር በሁለተኛ ደረጃ 262 አጠቃላይ ነጥብ መሰብሰብ የቻለው ሲዳማ ቡና ሆኗል። ከዚህ በፊት በነበረው የውድድር ዓመት ብዙም ውጤታማ ያልነበረው ክለቡ ፣ በዘንድሮው ውድድር ራሱን በሚገባ አጠናክሮ በመቅረብ ውጤታማ መሆን እንደቻለም ተነግሯል።በዓመታዊው ውድድሩ ጥሩ ግምት ከተሰጣቸው ክለቦች አንዱ የሆነው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ181 አጠቃላይ ነጥብ ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል። አምና በነበረው ውድድር ላይ በ121 ነጥብ ሁለተኛ በመሆን ማጠናቀቃቸውም ይታወሳል።ዓመታዊው ሻምፒዮና ለአጭር፣ መካከለኛ፣ የሜዳ ተግባራትና የርምጃ ተወዳዳሪ አትሌቶች የውድድር ዕድል ለመፍጠር፤ በክለቦች መካከል የውድድር ዕድል ለመፍጠር፤ ተተኪ አትሌቶችን ማፍራትን ዓላማ ያደረገ ነው። ለአሸናፊዎቹም በየደረጃው የተዘጋጀ የገንዘብ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፤ በግል አንደኛ ለወጣ 2000፣ ሁለተኛ ለወጣ 1500 እና ሦስተኛ ለወጣ 1000 ብር ሽልማት የሚበረከትላቸው ሲሆን፣ በቡድን 4 በ 400 ድብልቅ፣ 4 በ 800፣ 4 በ 1500 ሜትር እንዲሁም 4 በ 100 ሜትር ከብር 5000 እስከ 2000 የገንዘብ ሽልማት እንደየደረጃቸው ተበርክቶላቸዋል፡፡በውድድሩም ከክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ከሚገኙ 25 ክለቦች የተውጣጡ 706 አትሌቶች በሻምፒዮናው ላይ ተሳትፈዋል፡፡ ለተወዳዳሪዎች በድምሩ ከ200 ሺ ብር በላይ ሽልማት ተዘጋጅቷል። የኢትዮጵያ አጭር፣ መካከለኛ፣ እርምጃና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተጀመረው ታህሳስ 16 እስከ ታህሳስ 21 ቀን 2011 ዓ.ም ተጠናቅቋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 23/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "2775254ebc9e0bc4043adb42c4dae8de" } ]
b950f3291a996cd4aeee4b9736fe4a30
e713073883277182e3f12d501835f7f1
ኢትዮጵያዊው ብስክሌተኛ በቱር ደ ሩዋንዳ አሸነፈ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት የሚካሄደው ዓመታዊው ፔፕሲ የአዲስ አበባ ክለቦች አትሌቲክስ ቻምፒዮና ለ37ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም በመካሄድ ላይ ይገኛል።ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን የያዘው ውድድሩ በተለያዩ ርቀቶች የሩጫና ሜዳ ተግባራት አትሌቶችን በማፎካከር በርካታ ክብረወሰኖች እየተሻሻሉበት ይገኛል። በውድድሩ ሁለተኛ ቀን ውሎ ትናንት በተካሄደው የሴቶች አንደኛ ዲቪዚዮን አስር ሺ ሜትር ውድድር ክብረወሰን ተሰብሯል።በኢትዮጵያ ቻምፒዮና በአትሌት ለተሰንበት ግደይ 32፡10፡90 ተይዞ የነበረው የርቀቱ የኢትዮጵያ ክብረወሰን ዘንድሮ በአትሌት ዘይነባ ይመር በስድስት ሰከንድ ሊሻሻል ችሏል። በቻምፒዮናው ላይ በአንደኛ ዲቪዚዮን ከታቀፉ አምስት ክለቦች የተሳተፉ ሲሆን በሁለተኛ ዲቪዚዮን ከታቀፉ ሃያ ክለቦች የተውጣጡ በአጠቃላይ አንድ ሺ አትሌቶች ተሳታፊ ሆነዋል።ውድድሩ ክለቦች የአትሌቶቻቸውን አቅም ከመለካት ባሻገር በሃገር አቀፉ የአትሌቲክስ ቻምፒዮና ተሳታፊ ለመሆን የሚያስችላቸውን ምዘና የሚያደርጉበት እንዲሁም ስልጠናቸውን በመገምገም ራሳቸውን የሚያጎለብቱበት መድረክም መሆኑ ተነግሯል። ትናንት በተካሄደው የሁለተኛ ቀን ውሎ የተለያዩ የማጣሪያ እና የፍጻሜ ውድድሮች ተካሂደዋል።በሁለተኛ ዲቪዚዮን የ100 ሜትር ሩጫ በሁለቱም ፆታ የፍፃሜ ውድድሮች የተከናወነ ሲሆን፤ በሴቶች ትዝታ ደጋ ከአራዳ ክፍለ ከተማ እንዲሁም ሜሮን ተመስገን እና ፍቅርተ ሽፈራው ከዳሎል ክለብ ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል።በወንዶች በኩል ኤርሚያስ ሻጠው ከኮልፌ ቀራኔዮ ክፍለ ከተማ አንደኛ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያውን ወስዷል።የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲው አትሌት ሲሳይ አየሁ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ክለብ አትሌቱ ዘገየ ለገሰ ደግሞ ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል።በተመሳሳይ በ10ሺ ሜትር በወንዶችና ሴቶች ውድድር ፍጻሜያቸውን ሲያገኙ፤ በ1ሺ500 ሜትር፣ በአሎሎ ውርወራ እና በከፍታ ዝላይ አሸናፊ የሆኑ አትሌቶች የሜዳሊያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ነገ ቀጥሎ በሚውለው ቻምፒዮና የተለያዩ የፍጻሜ ግማሽ ፍጻሜና የማጣሪያ ውድድሮች የሚካሄዱም ይሆናል።በ5ኪሎ ሜትር በሴቶች እንዲሁም በ10ኪሎ ሜትር የወንዶች እርምጃ ውድድሮች ፍጻሜያቸውን ከሚያገኙት መካከል ይጠቀሳል።በሁለተኛ ዲቪዚዮን የሱሉዝ ዝላይ በሴቶች የማጣሪያ፣ በዲስከስ ውርወራ ወንዶች ግማሽ ፍጻሜ፣ በሁለቱም ጾታ የ400 ሜትር ፍጻሜ፣ 5ሺ ሜትር ሴት ግማሽ ፍጻሜ፣ 100ሜትር መሰናክል የሴቶች ግማሽ ፍጻሜ እና በ110ሜትር መሰናክል ሴት ግማሽ ፍጻሜ ይከናወናሉ።በአንደኛ ዲቪዚዮን ደግሞ በ100 ሜትር ሴትና ወንድ ግማሽ ፍጽሜ እንዲሁም በ110 ሜትር መሰናክል የወንዶች ግማሽ ፍጻሜ ውድድሮች በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሰረት ይካሄዳሉ። ይህ ዓመታዊ ቻምፒዮና በ1975 ዓ.ም መካሄድ የጀመረ ሲሆን፤ በፌዴሬሽኑ የተመዘገቡ ብዛት ያላቸው ክለቦች ሲሳተፉበት መቆየታቸውን መረጃዎች ያሳያሉ።ከ1991ዓ.ም ጀምሮም ፌዴሬሽኑ አቅሙን በማጎልበት ከሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ጋር በመተባበር ውድድሩ ለዓመታት በቋሚነት በመካሄድ ላይ ይገኛል። ፍጻሜያቸውን ባያገኙ ውድድሮች በቀዳሚነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የወርቅ፣ ብርና ነሃስ ሜዳሊያ የሚበረከትላቸው ይሆናል።ውድድሩ ከትናንት በስቲያ የተጀመረ ሲሆን በመጪው እሁድ 22/2012 ዓ.ም የሚጠናቀቅም ይሆናል። በቻምፒዮናው ከ1ሺ በላይ አትሌቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፣ ኢትዮጵያዊው ብስክሌተኛ በቱር ደ ሩዋንዳ አሸነፈ በሩዋንዳ በተካሄደ የ‹‹ቱር ደ ሩዋንዳ›› የብስክሌት ውድድር ኢትዮጵያዊው ሙሉ ኃይለሚካኤል አሸነፈ። ብስክሌተኛው 120 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በሸፈነውና ከዋና ከተማዋ ኪጋሊ ወደ ሁዬ ዲስትሪሲ የነበረውን ርቀት ለመሸፈንም 3ሰዓት ከ3ደቂቃ ከ21 ሰከንድ የሆነ ጊዜ እንደፈጀበት ዘ ኒው ታይምስ ዘግቧል።ለ12ኛ ጊዜ የሚካሄደው ውድድሩ እስከ መጪው እሁድ በተለያዩ ፉክክሮች የሚቀጥል ይሆናል። አትሌቶች ለቻምፒዮናው አልፈዋል ሰባት ዙሮች ያሉት የዓለም የቤት ውስጥ የዙር ውድድር የተጠናቀቀ ሲሆን ለዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና በቀጥታ ማለፍ የቻሉት 11 አትሌቶችም ተለይተዋል።ከእነዚህ አትሌቶች መካከልም የ3ሺ ሜትር ተወዳዳሪው ጌትነት ዋለ በወንዶች እንዲሁም በሴቶች ጉዳፍ ጸጋዬ 1ሺ500 ሜትር ማለፋቸውን ያረጋገጡ አትሌቶች ሆነዋል።ይሁን እንጂ የቻምፒዮናዋ አዘጋጅ የሆነችው ቻይና ከኮረና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ውድድሩ ወደ ሚቀጥለው ዓመት (እአአ 2021) መሸጋገሩ የሚታወስ ነው።በዙር ውድድሩ ቀዳሚ በመሆን ያጠናቀቁት አትሌቶች 20ሺ የአሜሪካ ዶላር ተሸላሚ መሆናቸውንም የዓለም አትሌቲክስ በድረ ገጹ አስነብቧል። ሊጉ ከሁለት ሳምንት በኋላ ይመለሳል የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ዙር የካቲት 29 እና 30/2012 ዓ.ም የሚጀመር መሆኑ ታውቋል።የግማሽ ዓመት ውድድር ከትናንት በስቲያ በቅዱስ ጊዮርጊስና አዳማ ከተማ መካከል በተደረገ ጨዋታ መጠናቀቁ ይታወቃል።ይህንንም ተከትሎ ሊጉን የሚመራው አቢይ ኮሚቴ ከሁለት ሳምንት እረፍት በኃላ ፕሪሚየር ሊጉ እንዲጀመር ውሳኔ ላይ መደረሱ ተረጋግጧል። የወርልድ ቴኳንዶ ቡድኑ አቀባበል ሰሞኑን ሞሮኮ ላይ ሲካሄድ በነበረው የወርልድ ቴኳንዶ የኦሊምፒክ ማጣሪያ ላይ ኢትዮጵያን የወከለው ቡድን ትናት አዲስ አበባ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፣የኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ፣ የአዲስ አበባ የወርልድ ቴኳንዶ አሰልጣኞች ማህበር እና የስፖርቱ ቤተሰብ ቡድኑ አዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ ሲደርስ ልዩ አቀባበል አድርጓል። ሰለሞን ቱፋ በማጣሪያ ውድድሩ በወርልድ ቴኳንዶ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለመሳተፍ የሚያስችለውን ውጤት ማስመዝገቡ ይታወሳል። ለሴት መምህራን ስልጠና ሊሰጥ ነው ለሴት የስፖርት ሳይንስ መምህራን የአሰልጣኝነት ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የ ‹‹ዲ ላይሰንስ›› አሰልጣኞች ስልጠና ለተመረጡ ሃገራት የሚሰጥም ይሆናል። ከሁሉም ክልሎች ለተወጣጡ 30 መምህራን የሚሰጠው ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 25/2012 ዓ.ም የሚቆይም ነው። ስልጠናው የሴቶች እግር ኳስ ልማትን ለማሳደግና ብቃታቸውን ለማሳደግ እንዲሁም አዳዲስ አሰልጣኞችን ለማፍራት የሚጠቅምም ይሆናል። በንድፈ ሃሳብና በተግባር የተደገፈው ስልጠናው በኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት አካዳሚ ኢንስትራክተር ሰላማዊት ዘርዓይ እና በተጋባዦች የሚካሄድ መሆኑንም የፌዴሬሽኑ የቴክኒክና ልማት ዳይሬክቶሬት በመረጃ ጠቁሟል። ስልጠናው ከተጠናቀቀ በኃላም እድሜያቸው 15 ዓመት በታች በሆኑ 10 የሴት ተማሪዎች ቡድን መካከል ውድድር ይካሄዳል። ቀነኒሳ በዓለም የግማሽ ማራቶን የሃገር አቋራጭ ንጉሱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በዓለም የግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና ለአሸናፊነት ይጠበቃል። ከቀናት በኃላ በፖላንድ በሚካሄደው ቻምፒዮና በማራቶን የሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ባለቤት የሆነው አትሌት ተሳታፊ እንደሚሆን የቢቢሲ ዘግቧል። አትሌቱ በውድድሩ ከእንግሊዛዊው አትሌት ሞ ፋራህ ፈታኝ ፉክክር ይገጥመዋል በሚል ቢጠበቅም፤ አትሌቱ በጉዳት ምክንያት የማይሳተፍ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የአሸናፊነት ግምቱን አግኝቷል። አዲስ ዘመን ረቡዕ የካቲት 18/2012
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27942
[ { "passage": "በኤርትራ አዘጋጅነት በብቸኝነት በቺቾሮ ስታዲየም እየተካሄደ የሚገኘው የሴካፋ ከ15 ዓመት በታች ዋንጫ ዛሬም ሲቀጥል ብሩንዲ እና ኬንያ አሸንፈዋል።ቀድመው ጨዋታቸው ያካሄዱት ኬንያ እና ሱዳን ሲሆኑ በጨዋታውም ኬንያ በሰፊ ውጤት 4-0 አሸንፋለች። ኬንያ ከወዲሁም በመገናኛ ብዙሃን ለዋንጫ የታጨች ቡድን ሆናለች። ቀጥሎ የተካሄደው እና ጥሩ እንቅስቃሴ ታይቶበታል የተባለው የሶማሊያ እና የብሩንዲ ጨዋታ ሲሆን በጨዋታውም ብሩንዲ 2-1 አሸንፋለች።ውድድሩ ነገም ሲቀጥል 8:00 ሰዓት ታንዛንያ ከ ዩጋንዳ በ10:30 ደግሞ ሃገራችን ኢትዮጵያ ከ ደቡብ ሱዳን ይገናኛሉ።", "passage_id": "47bae3e508e6cbe3e5ce0717404e30d0" }, { "passage": "በሩዋንዳ አስተናጋጅነት ከሐምሌ 12 ጀምሮ ሲደረግ የቆየው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ዛሬ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን 3ኛ ደረጃ ይዞ ጨርሷል።ከሁሉም ቡድኖች ከፍተኛውን የቻምፒዮንነት እድል ይዘው ዛሬ 09:00 ላይ ታንዛንያን የገጠሙት ሉሲዎቹ 4-1 ተሸንፈው እድላቸውን ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል። በ29ኛው ደቂቃ መሠሉ አበራ ለመሀል ሜዳ ከተጠጋ ርቀት የተገኘውን የቅጣት ምት በግሩም በቀጥታ በመምታት አስቆጥራ የመጀመርያውን አጋማሽ ኢትዮጵያ በመሪነት እንድታገድድ ረድታለች። ተከላካይዋ መሠሉ በተከታታይ 3 ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረች ሲሆን ሁለቱ ከቅጣት ምት የተገኙ ናቸው።ሉሲዎቹ በሁለተኛው አጋማሽ እጅግ ተዳክመው ሲቀርቡ ታንዛንያዎች በተሟላ የማጥቃት ኃይል ኢትዮጵያን የመከላከል አደረጃጀት አፈራርሰውታል። ኢትዮጵያ የተከላካይ ቁጥር በመጨመር ወደ ሜዳ ብትገባም ገና ሁለተኛው አጋማሽ እንደተጀመረ ምዋናሀምሲ ዑማሪ ግብ ካስቆጠረች በኋለ ነገሮች ለታንዛንያ ቀላል ሆነዋል። በ58ኛው ደቂቃ በግሩም የመልሶ ማጥቃት የተገኘውን ኳስ ሚንጃ ዶኒሲያ አስቆጥራ ታንዛንያን ወደ መሪነት ስታሸጋግር ስቱማይ አብደላህ በ62ኛው ደቂቃ ሦስተኛውን አክላለች። መደበኛው ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በተጨመረው ደቂቃ ደግሞ ፋቱማ ሙስጠፋ የማሳረጊያውን አስቆጥራ ጨዋታው በታንዛንያ አሸናፊነት ተጠናቋል።ውጤቱን ተከትሎ የ2016 ቻምፒዮኗ ታንዛንያ በ7 ነጥቦች በድጋሚ ቻምፒዮን ስትሆን ሁለሀኛ ደረጃ የመያዝ እድል የነበራት ሩዋንዳ በኬንያ በመሸነፏ እድሏን ሳትጠቀም ቀርታለች። በዚህም መሠረት ዩጋንዳ በ7 ነጥቦች በግብ ልዩነት ተበልጣ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኢትዮጵያ በ6 ነጥቦች ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ ለተከታታይ ውድድሮች የነሀስ ሜዳልያ ባለቤት ሆናለች።", "passage_id": "93ad0d6c25fb59c586913c88a664a6ca" }, { "passage": "በኤርትራ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የሴካፋ ከ15 ዓመት ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ኬንያ እና ዩጋንዳ ተጋጣሚዎቻቸውን በማሸነፍ የመጀመርያው የሴካፋ ዋንጫን ለማንሳት ተገናኝተዋል።በ7:30 የተካሄደው ጨዋታ የኬንያ እና የሩዋንዳ ጨዋታ ሲሆን የውድድሩ ጠንካራ ቡድን ኬንያ በመለያ ምት አሸንፋለች። በመደበኛው ሰዓት አንድ ለአንድ የተጠናቀቀው ጨዋታው ወደ መለያ ፍፁም ቅጣት ምት አምርቶ ኬንያ ሁለት ለአንድ አሸንፋለች።ቀጥሎ 10:00 የተካሄደው እና በኢትዮጵያዊው ዋና ዳኛ ለሚ ንጉሴ የተመራው የዩጋንዳ እና የብሩንዲ ጨዋታ በዩጋንዳ ስድስት ለባዶ አሸናፊነት ተገባዷል።ውድድሩ ዓርብ የሚጠናቀቅ ሲሆን የፍፃሜው ጨዋታም በዩጋንዳ እና ኬንያ መካከል ይደረጋል።", "passage_id": "293674d38c049940f1e6e9545c545d83" }, { "passage": "​የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የምድብ ለ የመጨረሻ ጨዋታ ዛሬ ሲካሄድ ኢትዮጵያ ከታንዛንያ ካለ ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡ጨዋታው የምድቡን የበላይ የሚለይ በመሆኑ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቶ የነበረ ሲሆን እንደተጠበቀው ጠንካራ ፉክክር አስተናግዶ ካለ ግብ ተጠናቋል፡፡ በውድድሩ ታሪክ የመጀመርያው ካለ ግብ የተጠናቀቀ ጨዋታ ሆኖም ተመዝግቧል፡፡በጨዋታው በሁለቱም በኩል ጥቂት የግብ ሙከራዎች የተስተናገዱ ሲሆን ኢትዮጵያ በሩዋንዳው ጨዋታ የነበራትን የበላይነት ለመድገም እንደተቸገረች ከስፍራው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ጨዋታው በአቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ የምድቡን አሸናፊ ለመለየት በወጣው እጣ ታንዛንያ አሸናፊ በመሆን የምድብ ለ የበላይ ሆና አጠናቃለች፡፡ ኢትዮጵያ በተመሳሳይ 4 ነጥብ ፣ 3 ግብ እና 1 የግብ ልዩነት በሁለተኝነት ስታጠናቀቅ ሩዋንዳ ካለምንም ነጥብ እና 2 የግብ እዳ 3ኛ ደረጃን ይዛለች፡፡የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች እሁድ ሲደረጉ የውድድሩ ትልቅ ጨዋታ በኬንያ እነና ኢትዮጵያ መካከል ይደረጋል፡፡ ሁለቱ ለዋንጫው ከፍተኛ ግምት ያገኙ ሃገራት በመሆናቸው ጠንካራ ፉክክር ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በሌላ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ታንዛንያ አስተናጋጇ ዩጋንዳን ትገጥማለች፡፡", "passage_id": "57f275ff2e11756abd69ff2939228b7b" }, { "passage": "ኢትዮጵያዊቷ ወጣት አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አስራ አምስት ኪሎ ሜትር ክብረወሰንን መጨበጥ ችላለች፡፡\nለተሰንበት ከትናንት በስቲያ በኔዘርላንድስ ‹ሰቨን ሂልስ ረን› በተባለ የጎዳና ላይ ውድድር ክብረወሰኑን ያሻሻለች ሲሆን ውድድሩን\nያጠናቀቀችበት ሰዓት 44፡20 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ከወር በፊት በዶሃው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በአስር ሺ ሜትር አስደናቂ ብቃት በማሳየት የብር ሜዳሊያ\nማሸነፍ የቻለችው ለተሰንበት በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና በወጣቶች ምድብ ለሁለት ተከታታይ ዓመታት ቻምፒዮን እንደነበረች ይታወሳል፡፡\nለተሰንበት የዓለም የአስራ አምስት ኪሎ ሜትር ክብረወሰንን ከአንድ ደቂቃ በላይ ያሻሻለች ሲሆን ይህ ክብረወሰን\nከሁለት ዓመት በፊት በኬንያዊቷ ጆይስሊን ጂፕኮስጌ 45፡37 በሆነ ሰዓት በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የተመዘገበ መሆኑን\nየዓለም አትሌቲክስ ድረ ገፅ ዘገባ አመልክቷል፡፡ የሃያ አንድ ዓመቷ አትሌት ለተሰንበት ከውድድሩ በኋላ ‹‹ገና ለውድድሩ ዝግጅት ሳደርግ በጥሩ አቋም ላይ እንዳለሁ\nአውቅ ነበር፣ በውድድሩም ላይ ምቾት ተሰምቶኛል፣ እውነቱን ለመናገር የቀድሞውን ክብረወሰን በምን ያህል ሰዓት እንዳሻሻልኩኝ ለማየት\nጓጉቼ ነበር›› በማለት የዓለም ክብረወሰን ስለመጨበጧ እርግጠኛ እንደነበረች ተናግራለች፡፡ ለተሰንበት ውድድሩን ከማሸነፏና የዓለም ክብረወሰን ከማሻሻሏ ባሻገር የመጨረሻዎቹን አስር ኪሎ ሜትሮች የሮጠችበት\nፍጥነት የአትሌቲክሱን ቤተሰብ ያስደነቀና ወደ ፊት ትልቅ ተስፋ እንዲጣልባት ያደረገ ነበር፡፡ ለተሰንበት የመጨረሻዎቹን አስር ኪሎ\nሜትሮች 29፡12 በሆነ ሰዓት ያገባደደች ሲሆን ይህም አልማዝ አያና በ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ የአስር ሺ ሜርት የዓለም ክብረወሰንን\nስታሻሽል ካስመዘገበችው 29፡17፡45 ሰዓት የፈጠነ ነው፡፡ የአስራ አምስት ኪሎ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ 2009 ላይ በተመሳሳይ ውድድር በጥሩነሽ\nዲባባ ተሻሽሎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ጥሩነሽ በወቅቱ የርቀቱን ክብረወሰን 46፡28 በሆነ ሰዓት ስታሻሽል ከእሷ በፊት ክብረወሰኑ\n46፡55 በሆነ ሰዓት በጃፓናዊቷ ካዮኮ ፉኩሺ የተያዘ ነበር፡፡ ጥሩነሽ ይህን ክብረወሰን ባስመዘገበችበት ውድድር በወንዶች ባለቤቷ\nአትሌት ስለሺ ስህን ከዩጋንዳዊው ኒኮላስ ኪፕሮኖ ጋር እስከ መጨረሻ አንገት ለአንገት ተናንቆ በተመሳሳይ ሰዓት በመግባት አሸናፊ\nእንደነበር አይዘነጋም፡፡ ለተሰንበት በነገሠችበት የዘንድሮው ዓመት ውድድር በስቶች ኬንያዊቷ ኢቫሊን ቺርቺር 46፡32 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ\nሆና ስታጠናቅቅ ሌላኛዋ ኬንያዊት ኢቫ ቺሮኖ 48፡14 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ፈፅማለች፡፡ በወንዶች መካከል የተካሄደውን\nውድድር የሃያ ሦስት ዓመቱ ዩጋንዳዊ ስቲፈን ኪሳ 41፡49 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችሏል፡፡ እሱን ተከትለው ኬንያውያኑ ኤድዊን ኪፕቶ\nበሁለት ሰከንድ ዘግይቶ ሁለተኛ፣ ሞሰስ ኮይች በ42፡05 ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል፡፡አትሌት ለተሰንበት ግደይ ክብረወሰን ከማሻሻል ባለፈ ያሳየችው አስደናቂ አቋም ተስፋ እንዲጣልባት አድርጓል፣አዲስ ዘመን ህዳር\n9 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ ", "passage_id": "9a8011dfb402f8a8d44870896ce6e824" } ]
5d70c3a9afd2482a8003cdd600b74660
bef3d8c90d701c4d690430dd47f82b87
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ፕሮጀክት ዓለም አቀፍ ኃላፊነቷን እየተወጣች መሆኗ ተገለጸ
 አዲሱ ገረመውአዳማ፡- ኢትዮጵያ የደን ሀብት መመናመንና የአየር ብረት ለውጥ እያስከተሉ ያሉትን ዘርፈ ብዙ ጉዳቶች ከግምት በማስገባት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ አገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በመዘርጋት ዓለም አቀፍ ኃላፊነቷን እየተወጣች መሆኗ ተገለጸ። በዘንድሮ ዓመትም ስድስት ቢሊዮን ችግኝ ለማፍላት መታቀዱም ተነግሯል።የአካባቢ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን እስካሁን የተተከሉ ችግኞች እንክብካቤና ጥበቃ ሥራዎችን እንዲሁም የ2013 በጀት ዓመት የችግኝ ተከላን የተመለከተ የውይይት መድረክ ትናንት በአዳማ ከተማ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የአካባቢ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ እንዳሉት፤ የደን ሀብት መመናመንና የአየር ብረት ለውጥ እያስከተሉ ያሉትን ዘርፈ ብዙ ጉዳቶች ከግምት በማስገባት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ አገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በመዘርጋት የአረንጓዴ ልማት ሥራን በማጠናከር እየተሰራ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ ኃላፊነቷን እየተወጣች መሆኑን ያሳያል። የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር እንደ ድርቅና ጎርፍ የመሳሰሉ የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመከላከል ይረዳል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ዘንድሮ የሚከናወነው የችግኝ ተከላ ከኢትዮጵያ አልፎ ጎረቤት አገራትንም ተደራሽ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ስድስት ቢሊዮን ችግኞችን ለማፍላት እንደታቀደና ከነዚህ ውስጥም አንድ ቢሊዮኑ ለጎረቤት አገራት እንደሚውሉ ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካና ታዳጊ አገራት ቃል ሆና በተለያዩ መድረኮች ስታነሳ እንደቆየች ሁሉ፤ ችግሩ በመድረክ ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ በተጨባጭ በአገር ቤት የሚሰራውን ሥራ በጎረቤት አገራትም ተግባራዊ በማድረግ ሚናዋን እንደምትወጣ አስታውቀዋል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ አረንጓዴ አሻራ በአገሪቱ የቆየውን የደን ሀብት ጥበቃ በማሻሻል ሌሎች የደን ሀብት ልማትን ለማሳደግና በእውቀት ለመምራት ያስችላል። በዚህም መንግሥት ኅብረተሰቡን በሰፊው በማሳተፍ ብሔራዊ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብርን ተግባራዊ ማድረግ ችሏል። በዚህም ባለፉት ሁለት የክረምት ወራት ብቻ ከ9 ቢሊዮን በላይ የደን የጥምር ግብርናና የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን መትከል ተችሏል። በተለይም ባሳለፍነው ዓመት የኮቪድ 19 ያስከተለውን ኢ-ተገማች ተጽዕኖ በመቋቋም ሥራው ተሳክቷል። ይህም ራስን ከቫይረሱ በመከላከል ማምረት እንደሚቻል ተሞክሮ የተወሰደበት አዲስ ሀሳብና ተግባር ሆኗል።ኮሚሽነሩ አክለውም፤ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመቋቋምና ተጋላጭነትን ለመቀነስ የሚያስችል የልማት ስልት ቀይሳ እየሰራች ትገኛለች ብለዋል። ይህንን በማድረግና አገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የደን ልማት ያለው ጠቀሜታ ከግምት በማስገባት ተጨባጭ ስኬት ማምጣት በሚያስችል መልኩ ወደ ሥራ መገባቱንም ጠቁመዋል። ደኖችን በተገቢው መንገድ ማልማት ለማህበራዊ ብልጽግና የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ውጤቶችን እንደ ተሞክሮ በመውሰድ እንዲሁም የቀጣይ ጊዜ ሥራዎችን በትኩረት መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል። ኮሚሽነሩ፤ እ.አ.አ በ2018፣ 15 ነጥብ 5 በመቶ ላይ የነበረውን የደን ሽፋን እ.አ.አ በ2030 ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ የተያዘውን ግብ ሊያሳካ በሚችል ሁኔታ ስትራቴጂካዊ ሥራዎች እንደተሰሩ ገልጸው፤ በአንድ ሰሞን ዘመቻ ተክሎ ገለል ማለት ብቻ ሳይሆን ለጽድቀቱም መረባረብ እንደሚገባ አሳስበዋል። በእስካሁኑ ክንውን አበረታችና አዎንታዊ ሁኔታዎች ቢታዩም አሁንም መሻገር የሚገባቸው በርከታ ክፍተቶች እንደተስተዋሉ በማንሳት፤ ሁሉም ለችግኞች ተከላ ያሳየውን ርብርብ ለእንክብካቤና ጥበቃ ተግባር መነሳሳት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በምክክር መድረኩ ሥራውን በአቢይና በቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ የሚመሩና የሚያስተባብሩ፣ ከፌዴራልና ከክልል መንግሥታት የዘርፍ መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፤ ባለፉት ጊዜያት የተከናወኑት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብራት ትምህርት የተወሰደባቸውና በቀጣይ በተሻለ ለመሥራት የሚያግዙ መሆናቸው ተመላክቷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38230
[ { "passage": "ሐምሌ 22 ቀን 2011 በዛሬው ዕለት 200 ሚሊዮን የዛፍ ችግኝ በመትከል ዕለቱን የአረንጓዴ አሻራ ቀን ለማድረግ በሚካሄደው ዘመቻ እስካሁን ድረስ 141 ሚሊዮን ችግኝ መተከሉ ተረጋግጧል።ኢትዮጵያ ለዓለም አረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ ካዘጋጁ አገሮች አንዷና የመሪነት ሚናዋን እየተጫወተች ያለች አገር ናት።ሀገሪቱ ‘የዜጎች የአረንጓዴ አሻራ ቀን’ በአንድ ጀምበር 200 ሚሊዮን ችግኞችን በመተከል ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ አዲስ ክብረወሰን ለማስመዝገብ አቅዳ ስትሰራ ነበር።በመሆኑም በዛሬው ዕለት በገጠርም ሆነ በከተማ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አገር ዜጎች በነቂስ ወጥተው እየተሳተፉ ይገኛሉ።ለክረምት ችግኝ ተከላ ዘመቻው ከ4 ነጥብ 7 ቢሊየን በላይ ችግኝ ተዘጋጅቷል።በኦሮሚያ 1 ነጥብ 9 ቢሊዮን፣ በአማራ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን፣ በደቡብ 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ችግኞች ተዘጋጅተዋል።", "passage_id": "011057ed5a6eedc0ca0f758604f47659" }, { "passage": "ኢትዮጵያ የአካባቢና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂን ተግባራዊ በማድረግ \"የ2017  ምርጥ ፖሊሲዎች ኦስካር አዋርድ\" ተብሎ የሚጠራውን ዓለም አቀፍ አሸናፊ በመሆን የወርቅ ተሸላሚ ሆናለች ።ኢትዮጵያ ሽልማቱን ያገኘችው የአካባቢ ተፈጥሮ ሀብት ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሃገራት ተብለው በተባበሩት መንግስታት የበረሀማነት መከላከል ምክርቤት ለውድድር ከታጩት ሃያ ስድስት የዓለም ሀገራት ፖሊሲዎች መካከል አንደኛ በመውጣት ነው፡፡ለመጨረሻ ዙር በዕጩነት የቀረቡትን ብራዚል፣ ቻይና፣ አውስትራሊያ፣ ዮርዳኖስና ኒጀርን በማሸነፍም የዓለማችን ምርጥ የመሬት ማገገም ፖሊሲ አሸናፊ መሆንዋን ምክርቤቱ በወርልድ ፊዩቸር ካውንስል ድረ ገጹ ይፋ አድርጓል።ኢትዮጵያ በርሃማነትን በመከላከልና የተፈጥሮ ሀብት ሥራዎችን የሚደግፍ ፖሊሲ ያላትና በዚህም ውጤታ ማበመሆኗ ለሽልማት አብቅቷታል ብሏል፡፡በተለይም በትግራይ ክልል ለዓመታት በተከነወኑት ውጤታማ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎች በአለም አቀፍ ደረጃ አሸናፊ በመሆን የወርቅ ተሸላሚ እንድትሆን እንዳደረጋት ነው የተገለጸው።ብዙ ህዝብ ትንሽ የአፈር መከላት የሚለው ትግበራ በትግራይ ክልል እውን መሆኑንና ይህም ሞዴል ሆኖ  በመገኘቱ ነው ሽልማቱ ለኢትዮጵያ የተበረከተላት ።ምርጥ የዓለማችን በረሃማነትን በመከላከል የዜጎችን ህይወት መቀየር የሚያስችል ፖሊሲ በሚል በሚሰጠው በዚህ ሽልማት ኢትዮጵያ ህብረተሰቡን በተለይም ወጣቶችን በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በማነሳሳት ውጤታማ የአካባቢ ጥበቃና በረሃማነትን የመከላከል ስራ መስራቷ ሞዴል አስብሏታል ፡፡በትግራይ ክልል በመሬት እቀባ ላይ የተመሰረተ እርሻ፣ የኢንዱስትሪ መር ፖሊሲን በሰፊ የህብረተሰብ ንቅናቄ መደገፍ፣ የወጣቶችን ጥያቄ ከህዝብ ብዛትና ከአፈር መከላት መቀነስ ጋር ማጣጣም፣ ዘላቂ ግብርናን በመተግበር፣ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የተሰሩት ስራዎች መሰራታቸውም ምክርቤቱ አድንቋል ።የዘላቂ ግብርና ተግባራትን በሚገባ በመተግበር በምግብ ራስን የመቻል ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አንዲመዘገብ ከፍተኛ ስራ መሰራቱን ተነስቷል።በመሆኑም ኢትዮጵያ የዓለማችን ምርጥ የመሬት ማገገም ፖሊሲ አሸናፊ በመሆን የወርቅ ተሸላሚ እንድትሆን አድርጓታል ነው ያለው ምክርቤቱ ።ብራዚልም ሲስተርን ፕሮግራም በሚል መርህ ሚሊዮን ድሃ ዜጎቿን በተለይም ሴሚያሪድ በሚባለው ግዛቷ በረሃማነትን በመከላከል አገግሞ ሰብል አብቃይ እንዲሆን በማድረግ ተጠቃሚ በማድረጓ የብር ሽልማት አግኝታለች ፡፡ቻይናም ላለፉት 15 ዓመታት በረሃማነትን መከላከል በሚል ፖሊሲ አውጥታ በመተግበር በረሃማነትን መከላከል በመቻሏና ጆርዳንም የደን መመናመንን በመከላከል በመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት ሞዴል የአካባቢ ጥበቃ ሥራ በመስራቷ የነሃስ ሽልማቱን በጋራ አግኝተዋል፡፡መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም በቻይና ኦርዶስ በሚደረገው 13ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ለውጥና በረሃማነት መከላከል አባላት ኮንፈረንስ ላይ በይፋ የሽልማቱ ስነ ስርዓት የሚካሄድ ይሆናል።ይህ ሽልማትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስጋት የሆነውን የአየር ንብርት ለውጥ አደጋ የተሸላሚ ሃገራትን ተሞክሮ በማስፋት በተቀናጀ መልኩ መከላከል እንዲቻል ማድረግ ነው ሲል ወርልድ ፊዩቸር ካውንስል በድረገጹ ገልጿል፡፡", "passage_id": "55a28aeeff17c329c5f5a5956bdb89b9" }, { "passage": " ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት በከፍተኛ ጥረት ውስጥ ከሚገኙ የአፍሪካ አገራት በግንባር ቀደምነት ትጠቀሳለች። ግብርና መር በሆነው የኢኮኖሚ ፖሊሲ በመመራት ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ያስመዘገበችው ተከታታይ የኢኮኖሚ እድገትም የዚህ ማሳያ ነው። በቅርቡ ደግሞ አገሪቱ የጀመረችው የለውጥ እንቅስቃሴ የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ጭምር የሳበና ለሁለንተናዊ እድገቷ መሠረት የጣለ ነው። በየዓመቱ በአማካይ በ2ነጥብ\n6 በመቶ እያደገ የሚገኘው ሕዝቧንም ከድህነት ለማውጣት የዘረጋቸው የልማት አቅጣጫ በተለያዩ አቅጣጫዎች እየተጓዘ ነው። ለምሳሌ የሚሌኒየም የልማት ግቦችን ለማሳካት የሄደችባቸው መንገዶችና የተገኙ ውጤቶች ለዚህ አንድ ማሳያ ናቸው። በዚህም የእናቶችና የሕፃናት ሞትን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ የተቻለ ሲሆን፣ አማካይ የዕድሜ ጣሪያንም በ20 ዓመት\nውስጥ ከ43 ወደ 64 ማሳደግ ተችሏል። የትምህርት ተደራሽነትም ላይ የተመዘገበው ውጤት በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ከእነዚህም ጎን ለጎን ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት በርካታ ሚሊየነር አርሶ አደሮችን ማፍራት ተችሏል። በቀጣይም ለግብርናው ልዩ ትኩረት በመስጠት በዘርፉ ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር መንግሥት 20 ቢሊዮን ብር ለግብአት መድቦ የግብርና ልማት ሥራዎች ማከናወን መጀመሩ ኢትዮጵያ ለፀረድህነት ዘመቻው የሰጠችውን ልዩ ትኩረት ያመላክታል። ከዚህም ጎን ለጎን ለዓለም ማህበረሰብ ጭምር አስጊ የሆነውን የአየር ንብረት ለውጥ ችግር ለመቋቋም ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችን በማከናወን ዓለምአቀፍ ትኩረትን መሳብ ችላለች። የተፋሰስ ሥራዎች፣ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ፣ የከተማና የመጠጥ ውሃ ሳኒቴሽን እንዲሁም የከተማ ሴፍቲኔት ፕሮግራሞችም የዚሁ አካላት ናቸው። በነዚህ ሥራዎች ላይ በተደረገው ርብርብም ባለፉት ጥቂት ዓመታት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እነዚህንና መሰል የልማት ሥራዎችን ለማከናወን በምታደርጋቸው ጥረቶችም የዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። በተለይ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ እና ለገጠር ሴፍቲኔት ፕሮግራም የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ድጋፍ ከፍተኛ ነው። ይሁን እንጂ በአገራችን በየዓመቱ ወደማህበረሰቡ የሚቀላቀለውን ከ2ሚሊዮን ያላነሰ ሥራ\nፈላጊ ኃይል ጥያቄ ለመመለስ የልማት ሥራዎችን አሁን ከተጀመረው በላይ በፍጥነት ማስኬድን የሚጠይቅ ነው። ለዚህ ደግሞ እንደ ዓለም ባንክ ዓይነት ትላልቅ የፋይናንስ ተቋማት ድጋፍ ወሳኝ ነው። ትናንት ዓለም አቀፉ የልማት ማህበር (አይዳ) ከ2021 እስከ\n2023 ለታዳጊ ሀገራት ለሚያደርገው ድጋፍ ከለጋሽ ሀገራት ገንዘብ ለማሰባሰብ የሚያስችለውን ስብሰባ በአዲስ አበባ ለማድረግ የመወሰኑም ምስጢር ማህበሩ በኢትዮጵያ የልማት እንቅስቃሴ ላይ ያለውን እምነት የሚያሳይ ነው። በዚህ ስብሰባ መክፈቻ ላይም የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በኢትዮጵያ በተደረጉ ድጋፎች በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የዓለም ባንክ በዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ወይም አይዳ በኩል ድጋፍ ከሚያደርግላቸው 75 ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን ድጋፉም በእርሻ፣ እንስሳት ሀብት ልማት፣ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ እና ልማት፣ የከተማ እና የመጠጥ ውሃ ሳኒቴሽን፣የገጠርና የከተማ ሴፍቲኔት ፕሮግራሞች ላይ ያተኮረ ነው። ከዚህም ባለፈ አይዳ ባለፉት ዓመታት በትምህርት፣ ጤና፣ ማህበራዊ ዋስትና፣ የፆታ እኩልነት፣ መልካም አስተዳደር ግንባታ እና ሌሎች ዘርፎች ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል። በቅርቡ ደግሞ በአገራችን ለኢኮኖሚያዊ ሽግግሩ ትልቅ ተስፋ በተጣለባቸው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት እንዲሁም በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በመንገድ እና ኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ያልተቆጠበ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከአምስት ቢሊዮን ዶላር ያላነሰ የልማት የፋይናንስ ድጋፍ በእርዳታና በብድር አግኝታለች። በአሁኑ ወቅትም በዓለም ባንክ ድጋፍ ከ13 ቢሊዮን ዶላር\nበላይ ወጪ የተደረገባቸው ፕሮጀክቶች እየተካሄዱ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ። ይህ ደግሞ አገሪቱ ለጀመረችው ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ነው። በአጠቃላይ እንዲህ ዓይነት ድጋፎች ኢትዮጵያ የጀመረቻቸውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ለማሳካትና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደቶችን በማፋጠን ሁለንተናዊ እድገት ለማስመዝገብ ከፍተኛ አቅም ይሆናታል። ለታዳጊ አገራት የሚውል ድጋፍ ማሰባሰብ ላይ ያተኮረው ጉባኤም በአዲስ አበባ መካሄዱ የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ የልማት እቅስቃሴ ላይ ያለውን ጠንካራ እምነት የሚያሳይ ነው። ይህ ደግሞ በቀጣይ ኢትዮጵያ የጀመረቻቸውን ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች በተሻለ ፍጥነት እንድታከናውን ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩም ባሻገር የዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ስለኢትዮጵያ አጠቃላይ የሪፎርም እንቅስቃሴ በቂ መረጃ ይዞ ድጋፍ እንዲያደርግ የሚያግዝ ነው። ከዚህም ባሻገር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አገሪቱ ያጋጠማት የውጭ ምንዛሪ እጥረት የተጀመሩትን ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች በሚፈለገው ፍጥነት እንዳታከናውንና የሪፎርም ሥራዎችም በተፈለገው ፍጥነት እንዳይጓዙ እንቅፋት የሚፈጥር ሲሆን የውጭ ምንዛሪ እጥረቱን ተከትሎ እያጋጠመ ያለው የዋጋ ግሽበትና የኑሮ ውድነትም እንዳይባባስ እንደ ዓለም ባንክ ዓይነት ትልቅ አቅም ያላቸው ተቋማት ድጋፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ይታመናል። በመሆኑም ኢትዮጵያ የጀመረችውን የሪፎርም ሥራዎች አጠናክራ ለማስቀጠልና የልማት ሥራዎችን ከዳር ለማድረስ ብሎም እድገቷን ለማፋጠን ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚደረግላት ድጋፍ ከፍተኛ እገዛ ያለው በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። እያንዳንዱ ዜጋም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እያደረገልን ያለውን ድጋፍና ይህንንም ተከትሎ የተገኘውን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ፊታችንን ወደልማት ማዞርና ፈጥነን ከድህነት መውጣት የእያንዳንዳችን ግዴታ በመሆኑ በየተሰማራንበት የሙያ መስክ ለሰላምና ለልማት እንትጋ።  አዲስ ዘመን ሰኔ 12/2011 ", "passage_id": "4c9dfe90e460c490727f4171310f30da" }, { "passage": "ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. በመላ አገሪቱ 200 ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት መርሐ ግብር ተይዟል፡፡ ‹‹አገራዊ የአረንጓዴ ልማት ድርጊት መርሐ ግብር›› በመባል በሚታወቀው አረንጓዴ አሻራ የማኖር ሥነ ሥርዓት፣ በችግኝ ተከላ የዓለም ክብረ ወሰን ለመስበር ዕቅድም ተይዟል፡፡ በመላ አገሪቱ በአጠቃላይ አራት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታስቦ እስካሁን 2.7 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ለማኅበራዊ ምርታማነት፣ ተጋላጭነትን ለመቋቋም፣ ለአየር ንብረት ተፅዕኖ መቀነስና መላመድ፣ ጤናን ለማሻሻል፣ ለዱር እንስሳት ከለላ፣ ለብዝኃ ሕይወት ከለላ፣ ለውኃ ማንፃትና ከለላ፣ እንዲሁም ለኢኮኖሚ ጠቀሜታ (ደንና ግብርና) ሲባል በሚከናወነው መርሐ ግብር በመላ አገሪቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ለችግኝ ተከላው 2.8 ሚሊዮን ጉድጓዶች መዘጋጀታቸው ተገልጿል፡፡ ነዋሪዎች በ116 ወረዳዎች በችግኝ ተከላው የሚሳተፉ ሲሆን፣ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡም የመትከያ ቦታ መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት ችግኞችን ሲተክሉ መሰንበታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከተለያዩ የውጭ አገር እንግዶች ጋርም ሲተክሉ ነበር፡፡ ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ደግሞ በደቡብ ክልል በወላይታ ዞን በሶዶ ከተማ ዳሞት  ተራራ ላይ፣ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ችግኝ እንደሚተክሉ ታውቋል፡፡ በምሥሉ ላይ የሚታየው የዳሞት ተራራ ሲሆን፣ ችግኞቹ ደግሞ በሶዶ የደንና ዕፅዋት ልማት ፕሮጀክት የፈሉ ናቸው፡፡", "passage_id": "c7d304018c47a16935952018ba248631" }, { "passage": "• የጠቅላይ ሚኒስትሩ 200 ሚሊዮን ችግኞች\n\n• የአየር ንብረት ለውጥ፤ የት ደረስን? \n\nየአረንጓዴ አሻራ ዘመቻው በአንድ ቀን 200 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የዓለምን ክብረ ወሰን መስበር እንዲሁም በአጠቃላይ 4 ቢሊየን ችግኞችን የመትከል ዓላማ ይዞ የተነሳ ነው።\n\nበዚህ የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ በአንድ ጀምበር ከ300 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በሕንድ ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን ኢትዮጵያ መስበሯ ተዘግቧል። ለመሆኑ የተተከሉት ችግኞች እንዴት ተቆጠሩ?\n\nይህንን ሂደት ሲከታተል የነበረው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር ሲሆን በሥሩም አንድ ቡድን ተቋቁሟል። ቡድኑ የችግኝ ተከላዎችን አቆጣጠራቸውንና ምዝገባቸውን የሚከታተል ነው።\n\nያነጋገርናቸው የዚህ ቡድን አስተባባሪ አቶ ኢምራን አቡበከር በትክክል መተከላቸውን ለመቆጣጠር ቀድሞ የተሠራ ሶፍት ዌር መኖሩን ይናገራሉ። እርሳቸውም ይህንን ሶፍት ዌር በመስራቱ ረገድ ሚና ነበራቸው።\n\nሶፍት ዌሩ በዛፍ መትከያ ቦታዎች ላይ የተከላውን ሂደት ለመቆጣጠር የተመደቡ ሰዎች ስልክ ላይ ብቻ የሚሠራ ሲሆን በአካል በመገኘት የቆጠሩትን ችግኝ ብዛት የሚያስተላልፉበት ሥርዓት አለው።\n\nበዚህም መሠረት በተመደቡበት ቦታ ላይ ምን ያህል ችግኞች እንደተተከሉ ቁጥሩን ሲያስገቡ ሶፍት ዌሩ በተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱትን አሃዞች በማጠቃለል እየደመረ ውጤቱን ይሰጣል። በመጨረሻ ላይም በአጠቃላይ በመላዋ ሃገሪቱ የተተከሉትን ችግኞች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ ያሳውቃል- ሶፍት ዌሩ።\n\nከዚህም ባሻገር ሌሎች የመቆጣጠሪያ መንገዶችን እንደተጠቀሙና ከ300 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውን አቶ ኢክራም ገልፀውልናል።\n\n• ምድር በአስፈሪ ሁኔታ እየሞቀች ነው\n\nከዚህ ቀደምም የተለያዩ የችግኝ መትከል ዘመቻዎች መከናወናቸው ይታወቃል። ሆኖም ምን ያህሉ ፀደቁ? የሚለው ላይ ባለሙያዎች ጥያቄ ያነሳሉ። የለም ኢትዮጵያ አካባቢ ልማት ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሞገስ ወርቁ ችግኝ ከመተከሉ በፊት ጥንቃቄ ያስፈልጋል ሲሉ ይጀምራሉ።\n\n\"መንግሥት ከዘመቻ ሥራ ወጥቶ የተጠና ሥራ መስራት አለበት\" የሚሉት አቶ ሞገስ ሰሞኑን ችግኞች በተተከሉባቸው ቦታዎች ላይ ሰዎች ግንዛቤው ሳይኖራቸው ቁጥር ላይ ብቻ ትኩረት ሲያደርጉ መታዘባቸውን ነግረውናል።\n\n\"አተካከላቸው ሳይንሱ የሚፈልገው ዓይነት አይደለም፤ አንዳንዱ ተከልኩ ለማለት ያህል ጣል አድርጎ የሚመጣ አለ\" ሲሉ በግድ የለሽነት ችግኝ እንደማይተከል ያስረዳሉ።\n\nችግኝ ያልተተከሉባቸው ቦታዎች እያሉ የተተከሉባቸው ቦታዎች ላይ መልሶ መትከልም ጠቃሚ እንዳልሆነ አቶ ሞገስ ያነሳሉ።\n\n\"በአንድ ጊዜ አገሪቱን በደን መሸፈን ይቻላል ብሎ ማሰብ አስቸጋሪ ነው\" የሚሉት አቶ ሞገስ በደንብ በባለሙያዎች በተጠና መልኩ፣ እቅድ ተይዞ፣ ይህን ያህል እንተክላለን ተብሎ፣ ቦታው ተለይቶ፣ የችግኞቹ ዝርያ ታውቆ፣ ችግኙም በወቅቱ ተዘጋጅቶ ሊካሄድ ይገባል ሲሉም ይመክራሉ።\n\nእስካሁን በነበረው ልምድ ችግኞች ሲተከሉ ለአካባቢው ተስማሚ የሆኑ ናቸው? አይደሉም? ብሎ ለመወሰን የሚያስቸግር መሆኑን በመግለጽ የተገኘው ሁሉ ነው ሲተከል የቆየው ብለዋል። \n\nይሁን እንጂ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ችግኞች ለመትከል የተደረገውን ይህን እንቅስቃሴና ዘመቻ ሳያደንቁ አላለፉም።\n\n ", "passage_id": "aab5916863a8e35346c03f3c263e9a28" } ]
df217caf62a70fd800476a8257c09393
f4dee03198c135906875984f4de9f4e2
በሶማሌ ክልል የተፈጠረውን ሰላም በመጠቀም በንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ ውጤታማ ሥራዎችን መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በሶማሌ ክልል የተፈጠረውን ሰላም በመጠቀም በንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ ውጤታማ ሥራዎችን መስራት እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አሳስበዋል። በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ከታኅሣሥ 17 እስከ 21 ቀን 2013 ዓ.ም የሚቆይ የኢንዱስትሪ፣ የግብርና እና የተፈጥሮ ሀብት ውጤቶች ኤግዚቢሽን ተጀምሯል። ኢቢሲ እንደዘገበው፤ በክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ በተዘጋጀው በዚሁ ኤግዚቢሽን ላይ የተገኙት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በሶማሌ ክልል የነበረው የሰብዓዊና የዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት ተወግዶ በሰላምና በፀጥታ ተጠቃሽ ክልል መፍጠር በመቻሉ የክልሉ የለውጥ አመራር ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።«ዓለማችንን ለሥልጣኔ ካበቋት ተግባራቶች መካከል አንዱ ንግድ ነው» ያሉት አፈ ጉባኤው፤ የአውሮፓ የኢንዱስትሪ አብዮትም ለዚህ ተጠቃሽ መሆኑን ገልፀዋል። ሰላም የንግዱን እና የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴውን ለማገዝ ቁልፍ ሚናን እንደሚጫወት በመግለጽም፤ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ባለሀብቶች በሶማሌ ክልል ኢንቨስት ቢያደርጉ አዋጭ መሆኑን ተናግረዋል። የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢብራሂም ኡስማን፣ ከዚህ ቀደም የነበረው የሰላም እጦት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የንግድና የኢንዱስትሪ አቅም በሚፈለገው ደረጃ ለመጠቀም አዳጋች አድርጎት እንደነበር ጠቅሰው፤ የክልሉ መንግሥት አሁን ላይ የተጀመረውን ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ከዳር እንዲደርስ የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ ባለሀብቶችን ለመሳብ በትኩረት እየሰራእንደሚገኝ አስታውቀዋል። የሶማሌ ክልል ሰፊ ያልታረሰ መሬት፣ የገፀ ምድርና የከርሰ ምድር ሀብት፣ የግብርና እና የእንስሳት ሀብት ባለቤት መሆኑን የገለጹት የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በበኩላቸው፤ ክልሉም እንዲህ ዓይነት ኤግዚቢሽኖችን በማዘጋጀትና በመሳተፍ የክልሉን የኢንዱስትሪና የንግድ ዘርፍ ማሳደግ ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ፣ ይህም ገቢ ምርትን ለመተካትና ወጪ ንግድን ለማሳደግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የሶማሌ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ጽ/ቤት ኃላፊ በሽር ሻፊ በበኩላቸው፤ የተዘጋጀው የኢንዱስትሪ፣ የግብርና እና የተፈጥሮ ሀብት ውጤቶች ኤግዚቢሽን የክልሉን እምቅ የኢንዱስትሪ እና የተፈጥሮ ሀብቶችን ለማስተዋወቅ እንደሚረዳ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38228
[ { "passage": " – ህዳር 29 በሶማሌ ክልል የሚከበረው 8ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል የክልሉን ልማት በማፋን በኩል ከፍተኛ -ቀሜታ እንዳለው የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አስታወቁ፡፡ በዓሉን በደመቀ ሁኔታ ለማክበርም ዝግጅቱ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ነው፡፡አፈ-ጉባዔው አቶ መሀመድ ኡመር ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ በዓሉ በክልሉ እንዲከበር መወሰኑ የተለያዩ ልማቶች እንዲካሄዱ ከመርዳቱም ባሻገር ልማቱ እንዲፋ-ን አስችሎታል፡፡በዓሉን ለማክበር ወደ ክልሉ የሚመ-# እንግዶችን በተገቢው ሁኔታ ለማስተናገድ የሚችሉ የተለያዩ የልማት ስራዎች መሰራታቸውን -ቁመው፤ የእንግዶች ማረፊያ፣ ስታዲየም፣ የፓናል ውይይት የሚካሄዱባቸው የስብሰባ አዳራሾችና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታ ተከናውኗል ብለዋል፡፡የተሰሩት ህንፃዎችና አዳራሾች የክልሉን የአየር ንብረት ግምት ውስ_ በመክተት  መሆናቸውን ገልፀው፤ የተለያዩ የአስፋልት ስራና የውስ_ ለውስ_ መንገዶችን በኮብልስቶን የማን-ፍ ስራ መከናወኑንም አፈ-ጉባዔው ተናግረዋል፡፡የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በልማት ታጅቦ እንዲከበር ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች መከናወናቸውን አፈ-ጉባዔው ገልፀው፤ የክልሉ ነዋሪዎችና ባለሀብቶች በንቃት እየተሳተፉ መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡በዓሉ የክልሉን ገፅታ ከመገንባቱ ባሻገር የሱማሌ ህዝብ እንግዳ ተቀባይነቱን ለተቀረው የሀገሪቱ ክልሎች የሚያስተዋውቅበት እለት ሆኖ እንደሚያልፍም አፈ ጉባዔው ተናግረዋል፡፡በዓሉ ከመድረሱ ቀደም ብሎ ዝግጅቱን ለማ-ናቀቅ መታቀዱን የገለፁት ደግሞ የክልሉ በዓል አከባበር ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በሽር አህመድ ለበዓሉ ዝግጅት ተብለው የሚካሄዱ የልማት ስራዎች መ=ረሻ ላይ ህብረተሰቡን ተ-ቃሚ የሚያደርጉ ናቸው ሲሉ መግለፃቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል፡፡", "passage_id": "2e4d11a3b798cab3dddeb854a3a4dae8" }, { "passage": "– በመጠናቀቅ ላይ ባለው የበጀት ዓመት በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በሠላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ። በክልሉ በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ በተሰሩ ስራዎችና ቀጣይ በሚኖሩ አቅጣጫዎች ዙሪያ የሚመክር ህዝባዊ ኮንፈረንስ ከባለፈው ማክሰኞ ጀምሮ በጅጅጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።በክልል ከሁሉም ወረዳዎች የተወከሉ 750 የሚሆኑ የሀገር ሽማግሌዎች፤ ወጣቶችና ሴቶች የኮንፈረንሱ ተሳታፊ ሲሆኑ፤ በ2005 ዓ.ም የተከናወኑ ዓበይት ተግባራትና ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም መመፍትሄዎቻቸው ቀርበዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር በኮንፈረንሱ ላይ በክልሉ እየተጠናቀቀ ባለው የበጀት ዓመት በትምህርት፣ በጤና፣ በእንስሳት ሀብት ልማት፣ በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ በመንደር ማሰባሰብና ተፋሰስ ልማት፣ በመንገድ ልማትና በጸጥታ ዘርፎች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አቅርበዋል።በዚሁ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደተናገሩት፤ በበጀት ዓመቱ ህብረተሰቡን የሠላም፤ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች ከዚህ ቀደም ከተከናወኑት ተግባራት የተሻለና አበረታች ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል።የክልሉ መንግስት ለትምህርት ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ሽፋን ከ85 በመቶ በላይ መድረሱን አቶ አብዲ ገልጸው፤ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥም በክልሉ 8 ሆስፒታሎች፤ 112 ጤና ጣቢያዎችና ከ900 በላይ የሚሆኑ ጤና ኬላዎች በሙሉ አቅም አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ምክንያት የጤና ሽፋኑን 83 በመቶ ማድረስ ተችሏል ብለዋል።እንዲሁም የክልሉን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ለማቃለል በተደረገው ጥረትም የ39 ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች የቁፋሮ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን፤ 28 ከተሞችም የንጹህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል። የአርብቶ አደሩን የእንስሳት ሀብት ጤንነትና ጥራት የተጠበቀ እንዲሆን ለማስቻልም በ68ቱም ወረዳዎች የእንስሳት የክትባትና ህክምና መድሃኒቶች በማዳረስ ከ10 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ እንስሳት የክትባት እንዲሁም 4ሺ400 ለሚሆኑ እንስሳት ደግሞ ህክምና መሰጠቱን አቶ አብዲ ተናግረዋል።በተለይ ክልሉ ከዚህ ቀደም ባሉት ዓመታት በገቢ አሰባሰብ ረገድ ችግር እንደነበረበት ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በዘንድሮው ዓመት የወረዳዎችን ገቢ የመሰብሰብ አቅም በመለየት በመሰራቱ በክልሉ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከእቅድ በላይ በ600 ሚሊየን ብር የሚበልጥ ገቢ መሰብሰቡን አስረድተዋል።እንዲሁም አርብቶ አደሩን በመንደር በማሰባሰብ የተሻለና የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና በዚህም ባለፉት አመታት አበረታች ውጤት መመዝገቡን ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።በበጀት ዓመቱ ከ33ሺ 324 በላይ አባውራዎችን በመንደር ለማሰባሰብ ታቅዶ ከ24ሺ በላይ አባውራዎችን ማሰባሰብ መቻሉንና የተለያዩ መቋቋሚያዎችና የማህበራዊ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ መደረጉን አቶ አብዲ ተናግረዋል።", "passage_id": "b1ad42dd3a7eeed6d53d01a73c8ec827" }, { "passage": "አዳማ፤\nየኦሮሚያ እና የሱማሌ ክልል ህዝቦች በሰላምና በፍቅር አብረው ለመኖርና ለመስራት ግንኙነታቸውን ማጠናከር በሚችሉባቸው ሁኔታ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚመክር የህዝብ ለህዝብ መድረክ በኦሮሚያ ክልል በአዳማ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በምክክር መድረኩ፤ የሁለቱ ክልል ወንድማማች ህዝቦች የነበራቸውን መልካም ግንኙነት በማጉላት ቀጣይ የጋራ ስኬትና ጉዞን ማስቀጠል በሚችሉበት ሁኔታ እንደሚመክር ይጠበቃል፡፡ ችግሮችን በባህላዊ የችግር ማስወገጃ እሴቶች መፍታት፣ በሁለቱ ክልል ህዝቦች ወሰን አካባቢ ሰላም ማረጋገጥ፣ የዜጎችን የመዘዋወርና የመስራት መብቶችን ማስከበር፣ ጥቂት ፖለቲከኞች በሚፈጥሩት አጀንዳ እየተከሰተ ያለውን የእርስ በእርስ መጠራጠር በማስወገድ፣ በመከባበርና በመደጋገፍ ስኬትን እንዲፋጠን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩ ይጠበቃል፡፡ ከክልሉ የኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በሁለቱ ክልሎች ባለስልጣናትና የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል የሚካሄደው የህዝብ ለህዝብ መድረክ የሁለቱ ክልል ህዝቦች እንደ ቀድሞው በሰላምና በፍቅር ግንኙነታቸው የሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ ያተኩራል፡፡ ሁለቱ ህዝቦች ረጅም ወሰን የሚካለሉ በመሆኑም በመካከላቸው ያለውን መልካም ግንኙነት በሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክሩም ነው የተገለጸው፡፡ ከዚህ ቀደም የተከሰቱ ችግሮች የሁለቱ ህዝቦች አጀንዳ አለመሆናቸውንና በተፈጠረው ችግር ማዘናቸውም ተገልጿል፡፡ ወደፊትም ተመሳሳይ ችግር እንዳይከሰት ጥንቃቄ ማድረግ ይገባልም ብለዋል፡፡ እንዲህ አይነት ድርጊት እንዲፈጸም የሚጥሩ ሃይሎችን በማጋለጥ ለመተባበር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ምክክር እንደሚደረግም ነው የተብራራው፡፡አዲስ ዘመን ሚያዝያ 23/2011", "passage_id": "427f08f4695240a5e6b56b94218e0048" }, { "passage": "የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል እና ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት የተቀናጀ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎችን በጋራ ለመስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ተወያዩ።በዚህ ወቅት የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሰብለጸጋ አየለ እንደተናገሩት፤ የክልሉ መንግስት በክልሉ የሚገኙ የባህል እና የቱሪዝም መስህቦችን ለማጎልበትና ለማሳደግ ከዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት አለው።በክልሉ የሚገኙ ተፈጥሯዊ፣ ታሪካዊና ባህላዊ ሀብቶችን ለተቀረው ዓለም በማስተዋወቅ ክልሉን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ እየሰሩ መሆኑን የገለጹት ቢሮ ሃላፊዋ፤ በዚህ ዙሪያም በቀጣይ በቂ ግንዛቤ እንዲፈጠር ከዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ጋር በጋራ እንሰራለን ብለዋል።ቢሮ ሃላፊዋ የዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት የተለያዩ የስራ ክፍሎችም ከኮርፖሬቱ ማኔጅመንት አባላት ጋር በመሆን ጎብኝተዋል።የዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ንጉሴ መሸሻ በበኩላቸው፤ ኮርፖሬቱ ከክልሉ መንግስት ጋር በጋራ ለመስራ በመመረጡ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።ኮርፖሬቱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ዶክመንታሪዎችና ፕሮግራሞች የክልሉን የባህል ስራዎች በተለያዩ ዶክመንታሪ ፊልሞችና ፕሮግራሞች በማስተዋወቅ በቅንጂት ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው፤ አሁንም የክልሉ ባህል እና እሴቶች ላይ ግንዛቤ የሚያጎለብቱ ስራዎችን እንሰራለን ብለዋል።", "passage_id": "8b241c9c8f000b09b25421220e90d427" }, { "passage": "አዲስ አበባ:- የኢትዮ-ኤርትራ የህዝብ ለህዝብ ብሎም የመንግስታቱን ግንኙነት ለማጠናከርና ወደላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ከቀድሞ በላቀ ደረጃ የክልሉ መንግስት በትኩረት እየሠራ እንደሚገኝ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ፡፡ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በተያዘው ዓመት የተጀመረው ዳግም የሁለቱ አገራት ግንኙነት ህወሓት ለግንባሩ ኢህአዴግ ባቀረበው ጥያቄና ባሳረፈው ውሳኔ መሠረት የተከናወነ እንደሆነ አስታውሰዋል፡፡ መንግስትም ሃሳቡን ተቀብሎ ተግባራዊ በማድረጉ የሁለቱ ሕዝቦች ዳግም ለመገናኘትና በርካታ ትሩፋትም ለማግኘት ችለዋል፡፡ የክልሉ መንግስት ከቀድሞ ጀምሮ ግንኙነቱን ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን በመግለጽ፤ በሰላም ሂደቱ ክልሉ ከፌዴራል መንግስት ጋር የተለየ አቋም እንዳለው በማድረግ የሚሰራጩ ወሬዎች ትክክል እንዳልሆኑና ተቀባይነት እንደሌላቸውም አስታውቀዋል፡፡ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የክልሉ መንግስት ሕገ፡መንግሥቱንና የፌዴራል ስርዓቱን በመጠበቅ ረገድ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወትም አያይዘው ጠቁመዋል፡፡ ሌሎች የሕዝቦችን አንድነት የሚያጠናክሩ ተግባራትም ይከናወናሉ ብለዋል፡፡ ዶክተር ደብረጽዮን፤ የክልሉ መንግስት የታችኛውን መዋቅር ዳግም የማደራጀት ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን አመላክተዋል። በክልሉ ያለውን ስራ አጥነት ለመፍታት፣ መልካም አስተዳደር ለማስፈንና የተሳለጠ አገልግሎት በመስጠት የህዝቡን ፍላጎት ለማርካት በክልሉ የታችኛውን የመንግስት መዋቅር ዳግም የማደራጀት ስራ ተጀምሯል ብለዋል። የክልሉ ሰላም ይበልጥ እንዲጠናከር ከመስራት አልፎ ለመልካም አስተዳደር ችግሮችና ለልማት ስራዎች እንቅፋት የሆኑትን ችግሮች ለመፍታት የተለየ ትኩረት የተሰጠ መሆኑን አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት በክልሉ ያለው አስተማማኝ ሰላም ኢንቨስትመንቱን ከማጠናከር ጀምሮ ለሌሎች ክልሎችና የውጭ አገር ዲፕሎማቶች ምሳሌ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። የቀበሌ መዋቅሩን የማጠናከርና አደረጃጀቱን የማስተካከል፣ የግብርና ስራውን የማጠናከር፣ የቁጠባ ባህልን በማዳበር ከተለያዩ ክልሎች ለተፈናቀሉት የመስሪያ ቦታና የገንዘብ ብድር እንዲያገኙ የማመቻቸት ስራ እየተሰራ መሆኑንም ዶክተር ደብረፅዮን ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ\n25/2011በሀፍቱ ገብረእግዚአብሔር ", "passage_id": "331e232309728fbf0f79aecbbd702df8" } ]
0a63d66d81ca8b9363da40f683886109
f137420a22a0b9375c0af5a9580ba342
ሚኒስቴሩ በፀጥታ ችግር ትምህርት ያልተጀመረባቸው አካባቢዎች ላይ ለማስጀመር እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
ዋቅሹም ፍቃዱአዲስ አበባ፡- በኮሮና ወረርሽኝ ዙሪያ ተገቢ ጥንቃቄ እየተደረገ በአብዛኛው አካባቢዎች ትምህርት ቢጀመርም በወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት ትምህርት ያልጀመሩ አካባቢዎችም ትምህርት እንዲጀምሩ እየሰራ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ገረመው ሁሉቃ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሰጡት አስተያየት፤ በአሁኑ ሰዓት ሁሉም አካባቢ በሚባል ደረጃ ትምህርት ተጀምሯል። ነገር ግን ከወቅታዊ የፀጥታ ችግር ጋር ተያይዞ በትግራይ ክልልና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን ትምህርት አልተጀመረም። በመሆኑም በእነዚህ አካባቢዎች ትምህርት ለማስጀመር የሚያስችሉ እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል።በዚህ ረገድ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ በተለይ በትግራይ ክልል ትምህርት ለመጀመር ጁንታው ከተመደሰሰ በኋላ ነባራዊ ሁኔታን የሚገመግም ኮሚቴ አዋቅሮ ወደ አካባቢው ልኳል። ሆኖም ግን ትምህርት ቤቶች በጁንታው ኃይል በመውደማቸው ምክንያት የመጠገን ሥራ ጊዜ መውሰዱ አይቀርም። በመተከል ላይም ተመሳሳይ ሥራ የሚሰራ ይሆናል።እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ፤ በትምህርት ቤቶች የኮሮና ወረርሽኝ ለመከላከል ለ25 ሚሊዮን ተማሪዎች 50 ሚሊዮን የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስኮች ለማቅረብ ታቅዶ ነበር። እነዚህን ማስኮችም በሁለት ሳምንት ውስጥ አምርተን አናቀርባለን ብለው ስምምነት የፈረሙት የአዳማና የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ግን በሁለት ሳምንት ቀርቶ በሁለት ወር ውስጥም ማቅረብ አልቻሉም። ይህ ደግሞ ሚኒስቴሩን ለትችት ዳርጎት ነበር።የመማሪያ ክፍሎችን በተመለከተም፣ አምና በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት ቤቶች እንደ ተዘጉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሚመራ አንድ መፍትሔ አፈላላጊ ተዋቅሮ ነበር። ይህ የቴክኒክና የሁኔታ አጥኚ ኮሚቴ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች እንዲሰሩ ወሰነ። በዚሁ መሰረት ደረጃቸውን ጠብቀው 700ሺህ የመማሪያ ክፍሎች ተገንብተዋል።ከእነዚህ ውስጥም 34ሺህ የሚሆኑ በኦሮሚያ የተገነቡ ናቸው።በሌላ በኩል፤ ከዚህ በፊት የግል ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደት የሚፈለገው ደረጃ የሚቆጣጠር አካል ባለመኖሩ ከአገሪቱ ሥርዓተ ትምህርት ባፈነገጠ መልኩ የመማር ማስተማር ሂደት ሲያከናወኑ መቆየታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ አሁን ግን ጉዳዩን የሚከታተል አካል ከመሰየሙም በተጨማሪ ቀጣዩ ዓመት አዲስ ሥርዓተ ትምህርት ሥራ ላይ ስለሚውል በአጠቃላይ በግልም ይሁን በመንግሥት ትምህርት ቤቶች በመማር ማስተማር ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች እንደሚቀረፉ ተናግረዋል።የ12ኛ ክፍል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መለቀቂያ ፈተናን በተመለከተም በ2012 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በኮሮና ምክንያት ፈተና ያልወሰዱ በአጠቃላይ 450ሺህ የሚሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘንድሮ ፈተና ይወስዳሉ። ይህንን ለማሳካት ለፈተናው ብቻ የሚውል ቪሳት ሌሎች አጋዥ መሳሪያዎች ተገዝተው 1ሺህ 184 ፈተና ጣቢያዎች ተቋቁመዋል። ለ270 ቴክኒሻኖችም ስልጠና ተሰጥተዋል። ለፈታኝ መምህራን 12ሺህ ላፕቶፖች ተዘጋጀቷል፤ ሁለት ትልልቅ ሰርቨሮችም በተገቢ ቦታ ላይ በመትከል ተማሪዎች እንዲለማመዱ ከ2008 እስከ 2011 ዓ.ም የተሰጡት የ12ኛ ክፍል ፈተናዎችም እዚያው ላይ ተጭነዋል። በትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ አማካኝነት በእርዳታ የተገኙ 450 ሺህ ታብሌቶች እስከ ታኅሣሥ 30 ወደ አገር ገብተው ለፈተናው የሚውሉ ሲሆን፤ ፈተናውም ጥር 30 የሚጠናቀቅ ይሆናል።የመምህራን የደመወዝ ስኬል ማስተካከያ ጋር ተያይዘው ከመምህራን የሚነሱ ቅሬታዎችን በተመለከተም የሥራ ግምገማና ደረጃ የተደረገው ደመወዝ ለመጨመር ሳይሆን ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘት ታስቦ እንደነበር የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ትምህርት ሚኒስቴርም ኃላፊነቱን ወስዶ መምህራን ተጠቃሚ በሚያደርግ መምህራንን ተጠቃሚ ለማድረግ መስራቱን ተናግረዋል። በዚህም ማስተካከያውን የሦስት ወር ለመምህራን ከፍሎ የቀሩት የሦስት ወር ክፍያ ለመክፈል ሲል ኮሮና በመከሰቱ ምክንያት ለተጠባባቂነት በመያዝ ሳይከፍል ቀርቷል። ካሁን በኋላ ግን ሁሉም ክልሎች ይህንን ደመወዝ ለመምህራኖቻቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲከፍሉ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38242
[ { "passage": "አዲስ አበባ፡- በኮቪድ 19 ምከንያት በተቋረጠው ትምህርት ዙሪያ የተማሪዎች ቀጣይ እጣ ፋንታ አገር አቀፉ ኮማንድ ፖስት በሚያስተላልፈውና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት የሚወሰን መሆኑ ተገለጸ። የትምህርት ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሯ ወይዘሮ ሀረጓ ማሞ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በቤት ውስጥ የሚሰጠው ትምህርት በሁሉም የአገሪቱ ክፍል በሚፈለገው ደረጃ ተደራሽ ነው ተብሎ ባይታመንም ብዙዎችን ከጭንቀት ለማላቀቅና ከትምህርት እርቀናል የሚል ስሜት እንዳይሰማቸው ለማድረግ አግዟል። ሆኖም ግን ትምህርቱና የቀጣይ ክፍል ዝውውር የሚወሰነው በኮሮና ወረርሽኝ መቆምና በመንግስት ውሳኔዎች መሰረት መሆኑን ተናግረዋል። \nየሬዲዮ እና የቴሌቪዥን የትምህርት ስርጭት በተለይ ክልሎች ላይ ሰፊ መሰናክል እንደሚያጋጥም የጠቆሙት ወይዘሮ ሀረጓ፤ በመብራትና በስርጭት ጥራት የተፈለገውን ያህል ትምህርቱን ማዳረስ አለመቻሉን ገልጸዋል። አሁን እየተሰጠ ያለው ትምህርት በምንም መልኩ ከመደበኛ ትምህርቱ ጋር የሚገናኝ አይደለም ያሉት ወይዘሮ ሀረጓ መደበኛውን ትምህርትም አይተካም ብለዋል። እንደ ዳይሬክተሯ ገለጻ፤ ትምህርቱ ሁሉንም ተማሪ የሚያቅፍበትና በእኩል ደረጃ ግንዛቤው የሚያዝበት ሁኔታ አለ የሚያስብል ስላልሆነ ከውጤት ጋር አያይዞ ለማስኬድ ከባድ ነው። የጥራት ጉዳይንም አደጋ ውስጥ ሊከተው ይችላል ብለዋል። \nቴሌቪዥንና ሬዲዮ የማያገኙ ተማሪዎችም ቀደም\n ሲል የተማሩትን ትምህርት ከደብተራቸው እና እጃቸው ላይ ያለውን መጽሐፍ በፕሮግራም እንዲያነቡ በማድረግ ቤተሰብ ሰፊውን ድርሻ ይዞ እየሰራ መሆኑ አስረድተዋል። \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ኃላፊው አቶ አበበ ቸርነት በበኩላቸው እንዳሉት፤የተማሪዎች የቀጣይ እጣ ፋንታ አገር አቀፉ ኮማንድ ፖስት በሚያስተላልፈውና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት የሚወሰን ነው።\nተማሪዎች ከመምህራን ጋር ያላቸው ግንኙነት ሙሉ ለሙሉ በመቋረጡ ቤተሰብ ኃላፊነቱን ወስዶ ልጆቹን በተቻለ መጠን መደገፍ እንዳለበትም አሳስበዋል። በኮሮና ምክንያት ትምህርቱ ቢቋረጥም በሁለት የሬዲዮ ጣቢያዎችና በማህበራዊ ድረገጾች ተማሪዎች አቅማቸውን የሚያጎለብቱበትና ትምህርቱን አውቀው የሚሄዱበት ስርጭት እየተላለፈ ይገኛል። \nከሰባተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች ሂሳብ፣ ባዮሎጂ፣ ፊዚክስና ኬሚስትሪ ትምህርት በቴሌቪዥን ይሰጣል፤ በኤፍኤም 94 ነጥብ 7 የሬዲዮ ጣቢያ ደግሞ ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ትምህርቱን እንዲያገኙ እየተደረገ ነው። በተመሳሳይ በቴሌግራምና ማህበራዊ ሚዲያዎች የስምንተኛና 12ኛ ክፍል ተማሪዎችን እስከ መፈተን የደረሱ ሥራዎች ተሰርቷል። የትምህርት ስርጭቱ በቋሚነት ቢከናወንም ተማሪዎቹ ራሳቸውን እንዲፈትሹ እንዲሁም ከትምህርቱ እንዳይርቁ ለማድረግ እንጂ ወደቀጣዩ ክፍል ለማዛወር እንዳልሆነ የሚናገሩት አቶ አበበ፤ ለቀጣይ ትምህርት ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ስለሚጠቅም በቀጣይም መሰጠቱ ይቀጥላል ብለዋል።\nአዲስ ዘመን ሰኔ 21/2012\nጽጌረዳ ጫንያለው", "passage_id": "e102ce8217f8fa294bd9bd69429845da" }, { "passage": "ከአንደኛ ክፍል በላይ ያሉ ሁሉም የግል ትምህርት ቤቶች፣ ከሰኞ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ፣ እንዲሁም ከአምስተኛ ክፍል በላይ ያሉ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ከኅዳር 28 ቀን 2013 ዓ.ም. የገጽ ለገጽ ትምህርት እንደሚጀምሩ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ትምህርት ቢሮው ዓርብ ኅዳር 18 ቀን 2013 ዓ.ም. በድረ ገጹ እንዳስታወቀው፣ በኮቪድ-19 ስታንዳርድ መሠረት ትምህርቱ የሚሰጠው በሁለትና በሦስት ፈረቃ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ በ1,900 ትምህርት ቤቶች ላይ በአራት ዙር የቅድመ ጥንቃቄና ዝግጅት፣ እንዲሁም ሰፊ ክትትልና ግምገማ መደረጉን የትምህርት ቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አዲሱ ሻንቆ ገልጸዋል፡፡በአሁኑ ጊዜ ከ1,687 በላይ ተጨማሪ ክፍሎች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን፣ የመማሪያ ክፍሎቹ ግንባታ እንደተጠናቀቀ ቀሪዎቹ የትምህርት ደረጃዎች ወደ ትምህርት መስክ ይመለሳሉ ብለዋል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመግታት በሁሉም ትምህርት ቤቶች በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ እንደሚቀመጥ የተገለጸ ሲሆን፣ ለመንግሥት ትምህርት ቤቶች ከ1.8 ሚሊዮን በላይ የፊት ማስክና ሳኒታይዘር፣ ከ700,00 በላይ የእጅ መታጠቢያ ሳሙናና የውኃ አቅርቦት መመቻቸቱን፣ እንዲሁም የግል ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመነጋገር ሁሉንም አስፈላጊ የሆኑ አቅርቦቶች ለተማሪዎች እንዲያዘጋጁ በቂ ዝግጅት መደረጉን አቶ አዲሱ አክለው ገልጸዋል፡፡የስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ኅዳር 24 እና 25 ቀን 2013 ዓ.ም. የሚሰጥ መሆኑን የገለጹት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፣ ተማሪዎቹ በቂ የሆነ የሞራልና የክህሎት ዝግጅት ማድረጋቸውን አስረድተዋል፡፡ በተያያዘ ዜና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ሥልጠና፣ ጥራትና የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ባለሥልጣን፣ በከተማው ውስጥ የሚገኙ 23 ትምህርት ቤቶችን የዕውቅና ፈቃድ መሰረዙን ገልጿል፡፡ፈቃድ የተሰረዘባቸው ትምህርት ቤቶች የተቀመጠውን መሥፈርትና ደረጃ ባለማሟላታቸው መሆኑን አስታውቋል፡፡", "passage_id": "6eb650ba17a704901313d0cb964d1cd4" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች በሚመለሱበት ወቅት ለትራንስፖርት እና ለሌሎች ችግሮች እንዳይጋለጡ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን ትምህርት ለማስቀጠል ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጋቸውን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡በዚህ መሰረትም የ2012 ዓ.ም ቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች ከፊታችን ጥቅምት 23 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲዎቻቸው በመመለስ የገፅ ለገፅ ትምህርት የሚጀምሩ ይሆናል፡፡በዚህ ወቅትም ተማሪዎች ለትራንስፖርት እና ለሌሎች ተያያዥ ችግሮች እንዳይጋለጡ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ነው የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ያስታወቀው፡፡በባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ይግዛው ዳኛ፣ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚመለሱ ተመራቂ ተማሪዎች አስተማማኝ የትራንስፖርት አቅርቦት መኖሩን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡ለዚህም የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የፌዴራል እና የክልል ቢሮዎች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ መከላከያ መንገዶችን ግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግም ለሁሉም መናኸሪያዎች አቅጣጫ መቀመጡን ነው የገለጹት፡፡በዚህ መሰረትም በመነኻሪያዎች ተጓዦች አካላዊ ርቀታቸውን እንዲጠብቁ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎችን እንዲጠቀሙ ይደረጋል ብለዋል፡፡በመነኻሪያዎች የሙቀት መለኪያ መሳሪያዎች መዘጋጀታቸውን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ በቫይረሱ የሚጠረጠሩ ተጓዦች ከተገኙም ለይቶ ማቆያ መኖሩን ጠቁመዋል፡፡ተማሪዎችም በጉዟቸው ወቅት በጤና ሚኒስቴር የተቀመጡትን የኮሮና ቫይረስ መከላከያ መንገዶች ገቢራዊ በማድረግ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡በመላኩ ገድፍ", "passage_id": "2aebbd2b34d3b385fee74c085f6b7c13" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመንን ለማስጀመር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የከተማዋ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የኮሮና ቫይረስን በመከላከል ትምህርትን በመደበኛ መልኩ ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ቢሮው ገልጿል። ከነሐሴ 20 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የግል ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን የመዘገቡ ሲሆን፤ በመንግሰት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ከመስከረም 5 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎችን የመመዝገብ ስራ እያከናወኑ ይገኛል። የከተማው ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ዳኞው ገብሩ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምዝገባ መጀመሩን በመግለፅ ተማሪዎች ጤንነታቸው ተጠብቆ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉም ከወላጆች፤ መምህራንና ርዕስ መምህራን ጋር ውይይት እንደሚደረግ ገልፀዋል። የኮሮና ቫይረስ መከሰት ከፍተኛ ተጽዕኖ ካሳደረባቸው ዘርፎች የሚጠቀሰው የትምህርት ዘርፉ ፤ ቫይረሱን በመካላከል ተማሪዎች ከትምህርታቸው ርቀው እንዳይቆዩ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ትምህርት የሚያገኙበትና የተለያዩ ምዘናዎች የሚሰሩበት ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል ብለዋል። በዚህም ምንም እንኳ ሁሉም ወደ ተግባር ገብቷል ባይባልም ተማሪዎች ከትምህርት እንዳይርቁ ያስቻለ መሆኑም ተጠቅሷል።የቢሮው ምክትል ሃላፊ እንደተናገሩት በተደረገው ጥረት የተማሪዎች አዕምሮ ከእውቀት እንዳይርቅ አግዟል፡፡ቀደም ሲል በእያንዳንዱ ትምህርት ቤት የቅኝት ስራ በማከናወን ምን ያህል የመማሪያ ክፍል እና የተማሪዎች መገልገያ ቁሳቁስ እንዳለ ጥናት መደረጉን ምክትል የቢሮ ሃላፊው ገልጸዋል።ሁሉም ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር ከመጀመራቸው በፊት የጸረ-ቫይረስ ኬሚካል ርጭት እንዲካሄድ ይደረጋል ያሉ ሲሆን ከጤና ባለሙያዎች ጋርም በቅርበት እየሰሩ እንደሆነም ነው ምክትል የቢሮ ሀላፊ ከፋና ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ የገለጹት። አሁን በመዲናዋ ትምህርትን ለማስጀመር የተደረገው ዝግጅት የተሻለ ነው የሚሉት ምክትል ሃላፊው መንግሰት በሀገር አቀፍ ደረጃ ትምህርት ይጀመር ሲባል ለመጀመር ቅደመ ሁኔታዎች ተጠናቀዋል።በሲሳይ ጌትነት", "passage_id": "ac6fdd3b86c5ba257cc3121a8f8176aa" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ መስከረም 14 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትን ትምህርት ለማስጀመር የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ መሰራቱ ተገለፀ፡፡የኮቪድ-19 ወረርሽኝን በመከላከል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትን መልሶ ለመክፈት የተደረጉ ዝግጅቶችና ለወረርሽኙ የተሰጡ ግብረ-መልሶችን አስመልክቶ የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡በመድረኩ ላይ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትን ትምህርት ለማስጀመር የሚያስችለው የቅድመ- ዝግጅት ስራ እየተሰራ እንደሆነ ተገልጿል፡፡በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር ጄኔራል ዶክተር ገነነ አበበ÷ አሰልጣኞችና ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች ለቫይረሱ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በፈረቃ በማሰራት የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል፡፡እነዚህም የንጽህና መጠበቂያ ቁሶችን በወቅቱ የማቅረብ እና በ8 ክልሎች ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ 1 ሺህ 58 በፔዳልና በሴንሰር የሚሰራ የእጅ መታጠቢያ ማሽን በማምረት ለኢንትርፕራይዞች ለማሸጋገር ተችሏል፡፡ከዚያም ባለፈ በአንዳንድ ተቋማት ሳኒታይዘር እና ሳሙና በማምረት ለህብረተሰቡ የመደገፍ ስራ ተሰርቷል፡፡ከ200 ሺህ በላይ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል በማምረት ለህብረተሰቡ የማቅረብ እንዲሁም ኢንተርፕራይዞችን በማብቃት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል እያመረቱ ለገበያ እንዲያቀርቡ በማድረግ ተጠቀሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ተችሏል ተብሏል፡፡በተጨማሪም በተቋማቱ ሀኪሞች የሚገለገሉበት አልባሳት መዘጋጀታቸውና ለቫይረሱ ተማሚዎች የሚያገለግል ጥራቱን የተጠበቀ 1 ሺህ 780 አልጋ በማምረት ለጤና ድርጅቶች ቀርቧል ነው የተባለው ፡፡ስልጠና ለማስጀመርም ስለቫይረሱ ያለው ግንዛቤ እያደገ መምጣት፣ ተቋማት በራሳቸው ወረርሽኙን ለመከላከል የሚረዱ መከላከያዎችን ማምረት መጀመራቸው፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በተመለከተ የአጠቃቀም ክህሎት መዳበሩ እና የሰልጣኞች ቁጥር ውሱን መሆኑ መልካም እድሎች ናቸው ተብሏል፡፡እንዲሁም የገጽ ለገጽ ስልጠና ለማስጀምርም የመማሪያ ክፍሎችን የማስተካከል፣ ወርክሾፖችን የማደራጀት እና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን የማሟላት ስራ በመከናወን ላይ መሆኑና ለአሰልጣኞች ግንዛቤ የመፍጠርና ቀሪ የብቃት አሀዶችን የመለየትና ፕሮግራም የማውጣት ስራ በአብዛኞቹ ኮሌጆች ተከናውኗል መባሉን ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡", "passage_id": "fe5373111dcc9c92d5df7106a8c7397f" } ]
1fb3456918fc5cea4f49c5e480d38113
7894b015fbd1563e1b6be55c927393a5
በ2022 የቱሪዝም ገቢን 23 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ እየተሰራ ነው
ለምለም መንግሥቱ አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ በ2022ዓ.ም ሰባት ነጥብ ሦስት ሚሊዮን የሚሆን ቱሪስት በመሳብ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ 23 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ እየሰራች መሆኑ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ተናገረ። በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የቱሪዝም ዘርፍ አማካሪ አቶ አህመድ መሐመድ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በአስር ዓመቱ መሪ ዕቅድ የመጨረሻ ዓመት በሆነው 2022 ዓ.ም ሰባት ነጥብ ሦስት ሚሊዮን የሚሆን ቱሪስት በመሳብ 23 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ ለማግኘት እየተሰራ ነው። በዚህም አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዷል። አቶ አህመድ እንደሚሉት፤ በሀገር ደረጃ አዲስ የሆነውን የቱሪዝም ኤክስፖርት በመተግበርና 26 በመቶ ድርሻ እንዲኖረው በማድረግ ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ በማድረስ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ወደ ትግበራ የተገባ ሲሆን፤ መሪ ዕቅዱም ለቱሪዝም ዕድገት ማነቆ የነበሩ ችግሮችን በመለየት ዘርፉን በሚያሳድጉት ላይ ቢሰራ የሚፈለግበት ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚቻል የሚያሳይ ነው። ይህ እንዲሆን ደግሞ ተወዳዳሪነትን መፍጠር፣ የመረጃ ልዕቀትን ማጎልበት፣ ጥናትና ምርምር ማካሄድ ላይ ትኩረት ማድረጉን የጠቆሙት አቶ አህመድ፤ በሀገሪቷ እየተገነባ ካለው ዕውቀት መር የኢኮኖሚ ሥርዓት ጋር ቱሪዝምን ለማስተሳሰር ጥራት ያለው ጥናትና ምርምር እንዲሁም ዕውቀት በማጎልበት ላይ ሥራዎች እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በትኩረት ከተሰራም ቱሪዝምን ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ ይቻላል የሚል እምነት መያዙን አስረድተዋል። በዓለም የቱሪዝም ገበያ ውስጥ እነ ቻይና፣ ጃፓን፣ ሩሲያ እና የመካከለኛ ምሥራቅ ሀገራት እየገቡ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ አህመድ፤ እነዚህን ማዕከል ባደረገ የቱሪዝም መዳረሻና አቅርቦት መኖር አለበት በሚል ዕቅዱ መቃኘቱንም አመልክተዋል። ተመልካች ብቻ ሳይሆን በሚጎበኘው አካባቢም ተሳትፎ ያለው ቱሪስት ነው የሚፈለገው ብለዋል። ቱሪዝም አካታች የቱሪዝም ገበያ ነው ያሉት አቶ አህመድ፤ ለሕግ የሚገዛ፣ በእውቀት የሚመራ፣ በቀጣሪና በተቀጣሪ መካከል መልካም ግንኙነት እንዲሰፍን የሚያደርግ ሥርዓት በመፍጠር የጎላ ሚና እንዲኖረው፣ በአነሥተኛ፣ በመካከለኛና በከፍተኛ የተደራጁ አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ዘርፉን እንዲቀላቀሉ፣ ሆቴል ቤቶችም እንዲስፋፉ እስትራቴጂው የሚያግዝ እንደሆነ አስረድተዋል። ዕቅዱ በተዘጋጀበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ ተገዳ ወደ አላስፈላጊ ጦርነት እንድትገባ ያደረጋት ነገር አዲስ ክስተት ነው ያሉት አቶ አህመድ፤ በአሁኑ ጊዜ ወደተረጋጋ ሥርዓት እየገባች በመሆኑ ዘርፉ መልሶ እንዲያንሰራራ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙኃንን ሳይቀር በመጠቀም የማስተዋወቅ ሥራው ይጠናከራል ብለዋል። በመንግሥት ሕግን ለማስከበር የወሰደው እርምጃ ዓለምአቀፍ ተቀባይነትን ለመጨመር እንደ አንድ የፖለቲካ አቅም መወሰዱን አቶ አህመድ ጠቁመው፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙኃንን ሳይቀር በመጠቀም ያደረገው እንቅስቃሴ በቱሪዝም ዘርፉ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችል ነበር ብለዋል። ነገር ግን ፖለቲካል ካፒታል የሚባለው የዲፕሎማሲ እና ሌሎችም ጥረቶች ግጭቱን በፍጥነት ለመቀልበስ እንዳስቻላትም አንስተዋል። የአስር ዓመቱ የቱሪዝም መሪ ዕቅድ ላይ በዘርፉ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ተሳታፊ የሆኑ አካላት፣ በከፍተኛ አመራር ላይ ያሉ የተቋሙ ሠራተኞች፣ በዘርፉ ላይ ከፍተኛ እውቀት ያላቸው የተካተቱበት አካላት ያዘጋጁትና ተተችቶ የዳበረ ሰነድና ለትግበራ የበቃ እንደሆነ አቶ አህመድ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38243
[ { "passage": ". 3 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጠራል አዲስ አበባ፡- የተለያዩ የኢኮኖሚ ጠቋሚዎች ሲታዩ በዘንድሮው በጀት ዓመት ኢኮኖሚው እስከ 9 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት የሚያስመዘግብ መሆኑን እንደሚያመለክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ገለጹ፡፡ የዘንድሮ የገቢ ማሰባሰቡ አፈፃፀም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት በ10 በመቶ ብልጫ እንዳለው እንዲሁም አስከ ቀጣዩ በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ ሦስት ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ሀገር አቀፍ እቅድ መያዙን አመለከቱ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት የ2011 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ የ2011 በጀት ዓመት እቅድ ኢኮኖሚውን ካጋጠሙት የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባትና ከተጫጫኑት ወቅታዊ ችግሮች እንዲያገግም ለማድረግ የተዘጋጀ ነበር፡፡ የ11 ወራት የሸቀጦች ንግድ አፈፃፀም ከተቀመጠው ግብ አኳያ ዝቅተኛ ከመሆኑ በስተቀር የኢኮኖሚው አጠቃላይ የፍላጎትና የአቅርቦት እንቅስቃሴው ሲታይ ማገገሙን የሚያመላክት መሆኑን መረጃዎች አሳይተዋል፡፡ በዚህም የዘንድሮው በጀት ዓመት ኢኮኖሚ እስከ 9 ነጥብ 2 በመቶ እንደሚያስመዘግብ ያመለክታል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 25/2011 ", "passage_id": "e7655ce57336498d45f405c02dc36b60" }, { "passage": "በቱሪስቶች አኃዝ ላይ ጥናት ያካሄዳልዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (አይኤፍሲ) ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ጋር በመተባበር ለዘርፉ ፍኖተ ካርታ ከማዘጋጀት ጀምሮ፣ የአቅም ግንባታ ድጋፎችንና የቱሪስት መዳረሻዎችን በማልማት ዘርፉ የሚያድግበትን የማማከር ድጋፍ ለመስጠት ስምምነት ፈረመ፡፡ ማክሰኞ የካቲት 26 ቀን 2011 ዓ.ም. ወሎ ሠፈር አካበቢ በሚገኘው የዓለም ባንክ ጽሕፈት ቤት በተደረገው ስምምነት ወቅት እንደተገለጸው፣ አይኤፍሲ ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ማሻሻያ ድጋፍ የሚሰጥባቸው መስኮች ላይ በአማካሪነት ይሳተፋል፡፡ ከአገር ውስጥና ከውጭ ባለሙያዎችን በማስመጣት በቱሪዝም መስክ መከናወን ስለሚገባቸው ማሻሻያዎች ምክረ ሐሳብ ይሰጣል፡፡ የአይኤፍሲ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ጁሞክ ጃንጉን-ዶኩንሙ ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሪት ሌንሳ መኮንን ጋር ስምምነቱን ሲፈራረሙ እንዳሉት፣ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዕምቅ አቅም ቢኖራትም እንደ ኬንያ፣ ሞሮኮ ወይም ደቡብ አፍሪካ ካሉት አገሮች አኳያ ብዙም አልተጠቀመችበትም፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለጻ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካይነት በየዓመቱ ከአሥር ሚሊዮን በላይ መንገደኞችን በማጓጓዝ በቱሪዝም መስክ ሰፊ አስተዋጽኦ ቢያደርግም፣ ከእነዚህ መንገደኞች ውስጥ ግን የአገሪቱን የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎች ለመጎብኘት የሚመጡት ከአሥር በመቶ ያነሱ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ከአንድ ሚሊዮን በላይ ጎብኚዎች ይመጣሉ እንደማለት ነው፡፡ በመሆኑም በትራንዚት አዲስ አበባን ረግጠው ከሚያልፉት አሥር ሚሊዮን መንገደኞች ውስጥ እስከ 20 በመቶ እንኳ (ሁለት ሚሊዮን ጎብኚዎች ማለት ነው) አገሪቱን መጎብኘት እንዲችሉ ቢደረግ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ያመላከቱት የአይኤፍሲ ዳይሬክተር፣ እንዲህ ያሉትን ለውጦች ሊያመጣ የሚችል ሥራ በመጪዎቹ ሦስት ዓመታት ውስጥ እንደሚከናወን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በዓለም ቱሪዝም ሰንጠረዥ መሠረት፣ በዓለም ላይ በቱሪስቶች ፍሰት አኳያ ከ189 አገሮች የኢትዮጵያ ደረጃ 89ኛ ነው ብለዋል፡፡ ይህ በየጊዜው እየተሻሻለ ቢመጣም፣ ኢትዮጵያ ካላት የቱሪዝም ሀብት አኳያ እንደ ደቡብ አፍሪካ፣ ሞሮኮ ወይም ኬንያ ከፍተኛ የጎብኚዎችን ቁጥር ማስተናገድ የምትችልበት አቅም አላት ሲሉ አክለዋል፡፡ ይህንን በማሻሻል ኢትዮጵያ ተጠቃሚ የምትሆንበት ፍኖተ ካርታ ይዘጋጃል ያሉት ዳይሬክተሯ፣ ኢትዮጵያ የምታስተናግዳቸው ቱሪስቶች ትክክለኛ አኃዝ የሚንፀባረቅበት የመነሻ መረጃም እንደሚዘጋጅና እስካሁን ሲጠቀስ የቆየው የቱሪስቶች አኃዝም በአግባቡ ከመነሻው እንደሚከለስ አስታውቀዋል፡፡የቱሪዝም ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ በበኩላቸው፣ የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ቱሪዝም በሚሰጠው ድጋፍ አማካይነት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን (በተለይም ‹‹ማይስ››) ጨምሮ የቱሪዝም መረጃዎችን በአስተማማኝ ሥርዓት ለመመዝገብ የሚያስችለውን የተመድን ‹‹ቱሪስት ሳተላይት አካውንት›› የተሰኘ አሠራር ለመተግበር በሚችልባቸው ሥራዎች ላይ አይኤፍሲ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ባስቀመጠው ነባር ዕቅድ መሠረት በ2017 ዓ.ም. በዓመት ከሦስት ሚሊዮን በላይ ቱሪስቶችን በማስተናገድ ከስድስት ቢሊዮን ዶላር ያላነሰ ዓመታዊ ገቢ እንደሚገኝ ይጠበቃል፡፡ ባለፈው ዓመት ከ3.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ያስገኘው ዘርፉ በአገሪቱ የፖለቲካ ትኩሳት ሳቢያ ጫና ውስጥ ገብቶ እንደቆየም ይታወሳል፡፡ በርካታ አገሮች የጉዞ ማስጠንቀቂያዎችን በማውጣት ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመጡ ሲያሳስቡ ቆይተዋል፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በፊትም አፋር ክልል ውስጥ በተከሰተ ግጭት ሳቢያ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የጉዞ ማሳሰቢያ ማውጣቱ፣ በአሁኑ ወቅት ከወጡ ማስጠንቀቂያዎች ብቸኛው እንደሆነ ይታሰባል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርካታ ቱሪስቶች ኢትዮጵያን እየጎበኙ ሲሆን፣ የቱሪዝምና የአገልግሎት ዘርፉም መነቃቃት እያሳየ መሆኑን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ", "passage_id": "3fe7cd4439fc1d1093573ba4cf91b69d" }, { "passage": "– በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት አገሪቱ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ633 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።በሚኒስቴሩ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አወቀ ጤናው ለዋልታ እንደገለጹት ገቢው የተገኘው የተለያዩ የአገሪቱን የመስዕብ ቦታ ከጎበኙት 629ሺ 050 የውጭ ሃገር ቱሪስቶች ነው።ሃገሪቷን የሚጎበኙ የውጭ ቱሪስቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የጠቆሙት አቶ አወቀ ከ2004 የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የቱሪስቶች ቁጥር በ8 በመቶ በገቢ ደረጃ ደግሞ 37 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ተናግረዋል። የቱሪስት ፍሰቱና ገቢው ሊጨምር የቻለው የአገሪቱን ባህላዊ ፤ተፈጥሮዋዊና ታሪካዊ ቅርሶችን የማስተዋወቅ ሥራዎች በመሰራታቸውና በ11 ዓለም ዓቀፋዊ የንግድ ትርኢቶች ላይ ተሳትፎ በመደረጉ መሆኑን አቶ አወቀ ተናግረዋል።  በአገሪቱ የተመዘገበው ተከታታይ የኢኮኖሚ ዕድገትና አሁን ያለው አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት አገሪቱን ተመራጭ  የቱሪስት  መዳረሻ እንድትሆን በማድረግ ለገቢው መጨመር የራሱ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተናግረዋል። በሃገሪቱ የሚገኙት ፓርኮች ለቱሪስቶች የሚሠጡትን አገልግሎት ለማሻሻል በ2005 የበጀት ዓመት 3 ሺ 866 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ላይ ጥገና መካሄዱን የጠቀሱት አቶ አወቀ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ 65 የቱሪስት ካምፖች ተገንብተው አገልግሎት በመሥጠት ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።የዘንድሮው አለም አቀፉ የቱሪዝም ቀን መስከረም 17 በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሚገኙ ታሪካዊ ሥፍራዎች በደመቀ ሥነ ስርዓት እንደሚከበር አቶ አወቀ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።", "passage_id": "50f6e0b2b3c8e5d9a72a00c45921742a" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አሁን ላይ የተጀመሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት ስራዎች ቱሪዝሙን በማነቃቃት ሀገራዊ ምጣኔ ሀብት ለማሳደግ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የምጣኔ ሃብት ጉዳዮች መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ንጉሴ ስሜ፥ አሁን ላይ የተጀመሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት እና የማሳደግ ስራዎች ኢንቨስትመንትን እንደሚያነቃቃ ገልጸዋል።የተጀመሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት እና ማሳደግ ስራዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ያነሱት ዶክተር ንጉሴ፥ በተለይ ስራዎቹ በሚሰሩበት አካቢዎች የሚፈጠረው የኢንቨስትመንት መነቃቃትን ተከትሎ የሚገኙ መልካም አጋጣሚዎችን በቀዳሚነት ተመልክተዋል።ሌላኛው የምጣኔ ሃብት ባለሙያ እና ሶሾ ኢኮኖሚክ ጉዳዮች ተንታኝ ዋሲሁን በላይ እንዳሉት፥ ሃገር በቀል እውቀቶች ተግባራዊ የተደረጉበት እና የሃገሪቱን ማህበረ ፖለቲካ በአንድ ስፍራ ለማስጎብኘት አሁን ላይ የተደረገዉ ሙከራ የበርካቶችን ቀልብ እንዲስብ የሚያደርግ ነው።በተጨማሪም ይህ የሀገርን ሃብት የሀገር ልጅን ባሳተፈ መልኩ የማልማት እንቅሰቃሴ፣ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ማጠናቀቅ እና ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።አካባቢን እና ተፈጥሮን ከመንከባከብ ጋርም ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት እና ማሳደግ ስራ ፓርኪንግ ዴቨሎፕመንት፣ በዜጎች ጤናማ ህይዎት ላይ አወንታዊ ሚና እንዳለዉም ገልፀዋል።እንዲሁም ባለሙያዎቹ መሰል ሀገራዊ ፕሮጀክቶች የመንግስትና ማህበረሰብን ግንኙነት ለማጠናከር ወሳኝ ሰለመሆናቸው ጥናቶችን ዋቢ አድርገዉ የተናገሩ ሲሆን፥ ህዝብ በመንግስት ላይ ያለውን አመኔታ ከፍ እንደሚያደርግም አንስተዋል።በአወል አበራ", "passage_id": "3bd6ccc87cc532ccb25c0085411a0cfb" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያን የጎብኚዎች መዳረሻ ስፍራዎች በኦን ላይን ማስተዋወቅ መጀመሩን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ሚኒስቴሩ የቱሪዝም ዘርፉ ኮሮና ወረርሽኝ ያሳደረበትን ተጽዕኖ የሚያገግምበትን አቅጣጫ በማስቀመጥ 3 በሊዮን ዶላር ለማግኘት ማቀዱን በሚኒስቴሩ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ተወካይ አቶ እንደገና ደሳለኝ ለኢዜአ ገልጸዋል፡፡በተጠናቀቀው በጀት አመት በኢትዮጵያ ኮሮና ባስከተለው ቀውስ ከዘርፉ ለማግኘት ከታቀደው ሁለት ሦስተኛውን ገቢ ብቻ ማሳካት መቻሉንም ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል፡፡ባለፈው በጀት አመት ኢትዮጵያን ይጎበኛሉ ተብለው ከተጠበቁ 1 ሚሊየን በላይ የውጭ ሃገር ጎብኚዎች ውስጥ 541 ሺህ ሰዎች ብቻ ጎብኝተዋል፡፡ችግሩ የጉብኚዎችን ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ከመቀነሱ ምበተጨማሪ ቆይታቸውን አሳጥረው ወደ መጡበት እንዲመለሱ ማድረጉንም አንስተዋል፡፡ወደዚህ ለመምጣትም የሆቴል ምዝገባና መሰል ነገሮችን የጨረሱ ጎብኚዎች ባሉበት እንዲቆዩ ተገደዋልም ነው ያሉት፡፡በበጀት ዓመቱም 2 ነጥብ 71 ቢሊየን ዶላር ከጎብኚዎች መገኘቱንም ተናግረዋል፡፡በሃገር ውስጥ በቱሪዝም ዘርፉ የሚተዳደሩ ተቋማትንና ሰዎችን ለመደገፍ መንግስት 3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወለድ አልባ ብድር መስጠቱንም ጠቅሰዋል፡፡በያዝነው በጀት አመት ኢትዮጵያን ከሚጎበኙ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን የውጭ ሃገር ጎብኚዎች ከ3 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት መታቀዱንም አስረድተዋል፡፡ፎርብስ መጽሔት ከኮሮና በኋላ ሊጎበኙ ከሚገባቸው 10 ሃገራት መካከል ኢትዮጵያን በሰባተኝነት ማስቀመጡ ይታወሳል፡፡", "passage_id": "74f791a87833ae2efd4c2255c0052363" } ]
f206cd851026f5eba58d1e7764878854
a18db7eef3546008a2beb50ad54ddd72
በጁንታው ላይ የተመዘገበው ድል በተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩ ግድያዎች በማስቆም እንዲደግም የደባርቅ ከተማ ነዋሪዎች ጠየቁ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- የአገር መከላከያ ሰራዊት በትህነግ ጁንታ የጥፋት ቡድን ላይ ያስመዘገበውን ድል በተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩ ግድያዎችን በማስቆም እንዲደግመው የደባርቅ ከተማ ነዋሪዎች ጠየቁ። በሕገ ወጡ የትህነግ ቡድን ታግተው መከራ እና ስቃይ ያሳለፉትን የሰራዊት አባላት ተቀብለው ለተንከባከቡት የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች የምስጋና እና የእውቅና መርሃ ግብር በደባርቅ ከተማ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ወቅት እንደተገለጸው፤ በሕገ ወጡ የትህነግ ቡድን በሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ በፈፀመው አስነዋሪ ድርጊት የኢትዮጵያውያንን ስሜት ክፉኛ ጎድቶ ነበር። ሕግ በማስከበሩ ርምጃም በአራቱም ጫፍ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመከላከያ ጎን መቆሙን ሲገልፅ ቆይቷል። ጥቃቱ በተፈፀመባቸው የትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች የሚገኙ ሕዝቦች ደግሞ መከላከያ ኃይሉ ከተሰነዘረበት ጥቃት አገግሞ ለድል እንዲበቃ  ታሪክ የማይሽረው አኩሪ ገድል ፈፅመዋል።ትህነግ በሰነዘረው ጥቃት ቀጥተኛ ዒላማ መከላከያ ሰራዊት እና የአማራ ሕዝቦች በመሆናቸው ይህንን ጥቃት ከመከላከል አልፎ በተለያየ የጉዳት ደረጃ ላይ የነበሩ የመከላከያ እና የፌዴራል ፖሊስ አባላትን ተቀብሎ አስተናግዷል። በሕገ ወጡ ቡድን አፈና ደርሶባቸው ለሳምንታት በርሃብ፣ በውሃጥም እና ድካም በሕይወት እና ሞት መካከል የነበሩት የመከላከያ አባላት በበየዳ እና ጠለምት ወረዳዎች በኩል አድርገው ወደ ሰሜን ጎንደር ዞን አካባቢዎች ሲገቡ ሕዝቡ በፍቅር ተቀብሎ አስተናግዷቸዋል።የአማራ ሕዝብ ለሰራዊቱ ላደረገው እንክብካቤ፣ ፍቅር እና ድጋፍ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ጎንደር እና ምዕራብ ጎንደር ዞን ኮማንድ ፖስት የምስጋና እና እውቅና መርሃ ግብር ከትናንት በስቲያ በደባርቅ ከተማ አዘጋጅቷል። በምስጋና መርሃ ግብሩ የተገኙት የደባርቅ ከተማ ነዋሪዎችም የሀገር መከላከያ ሰራዊት የትህነግን የጥፋት ቡድን በማያዳግም መልኩ በማስወገድ ያሳየውን አኩሪ ጀብዱ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚፈጠሩ የሰላም መደፍረስ ችግሮችን እንዲያስቆም ጠይቀዋል። «የትናንቱ ድል የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድል ነው» ያሉት የደባርቅ ከተማ ነዋሪ አቶ መኳንንት ደሳለኝ፤ ጦርነቱ ቢያልቅም ዛሬም የተልዕኮ ፈፃሚዎች ሴራ ፈፅሞ አልከሰመም ብለዋል። በመተከል እና በሌሎች አካባቢዎች ያለውን ግድያና መፈናቀል ማስቆም የሰራዊቱን ተልዕኮ የሚሻ በመሆኑ የትናንቱን ገድላችሁን በመፈፀም ኢትዮጵያን መታደግ ይኖርባችኋል ሲሉም ጠይቀዋል።ሰራዊቱ ከልጆቻችን መካከል እንደ አንዱ ነው ያሉት ሌላዋ የደባርቅ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ እናንየ መስፍን፤ ከደረሰበት የስነ ልቦና ስብራት አገግሞ እና ተልዕኮን በብቃት ፈፅሞ በዚህ መልኩ ለምስጋና መገኘታችን አስደሳች ነው ብለዋል። የሰሜን ሕዝብ ያሳየው ፍቅር፣ እንክብካቤ እና ጀግንነትም አማራ ጠላቶቹ እንደሚሉት ሳይሆን ለኢትዮጵያ አንድነት ያለውን ጥልቅ ፍቅር ዳግም ያስመሰከረ በመሆኑ ኮርተንበታል ብለዋል። በዕለቱ ለምስጋና የተገኙት የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትም ሕዝቡ በሕግ ማስከበር ርምጃው ያደረገውን ገድል ታሪክ እና የመከላከያ ኃይሉ ዘላለም ሲዘክረው እንደሚኖር መግለጻቸውን የዘገበው የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ነው።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38303
[ { "passage": "ከአዲስ አበባ ወደ ሰቲት ሑመራ ከተማ የ68 ነጋዴዎች ንብረት ጭነው ይጓዙ የነበሩ ሁለት መኪኖች፤ ደባርቅ ከተማ ሲደርሱ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ንብረቶቹን እንዲራገፍ አድርጓል ሲሉ ንብረት የተያዘባቸው ነጋዴዎች ቅሬታ አቀረቡ።የደባርቅ ከተማ ፖሊስ አዘዥ ዋና ኢንስፔክተር ውቤ ተዘራ ንብረተቹን በቁጥጥር ሥር የዋሉት በቡድን ሆነው ንብረቱን ለማቃጠልና ለመዝረፍ ከሞከሩት ሰዎች ለማዳን ነው ብለዋል።። ", "passage_id": "95a0dd20a7725ac1cd91bf13fa1ec2fc" }, { "passage": "ሰሞኑን በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች አንዳንድ ወረዳዎችና ቀበሌዎች አካባቢ በተከሰተው  ግጭት  ምክንያት  ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ጥልቅ  ሃዘን  እንደተሰማው የአማራ  ብሔራዊ  ክልላዊ  መንግሥት  ገለጸ ።የአማራ ብሔራዊ  ክልላዊ  መንግሥት በትናንትናው ዕለት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ሰሞኑን በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት በሕይወት ፣ በአካልና ንብረት  ላይ ጉዳት  ደርሷል ፣ በአካባቢውም አለመረጋጋት ተፈጥሯል ብሏል ።በአማራ ክልል በህዝብ  የሚነሱ ትክክለኛ ጥያቄዎችን በመፍታት የተጀመሩት እንቅስቃሴዎችን ሥር እንዲሰዱ ለማድረግ መጠነ ሰፊ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ መግለጫው አመልክቷል ።በክልሉ ህዝብ እየታየ ያለውን ለውጥ እንዳይቀለበስ በተለያዩ መልኩ መልዕክቶችን  ቢያስተላልፍም ለውጡን የማይፈልጉ ኃይሎች  በየጊዜው በሚሸርቡት እንቅፋቶች አሁንም ፈተና መሆናቸው እንዳልቀረ  መግለጫው አትቷል ፡፡      የለውጡ አደናቃፊዎች ከሚጠቀሙባቸው ስልቶች መካከል ሕዝቡንና አመራሩን በልዩ ልዩ መልኩ በመከፋፈል፣ ለውጡን በማጣጣል፣ ሕዝቡ በበርካታ አጀንዳዎች እንዲጠመድ፣ ሥርዓተ አልበኝነት እንዲነግስና ለውጡ ፋይዳ ቢስ መሆኑን  ለማሳየት  የሚያስችሉ  እንቅስቃሴዎችን በማድረግ  ላይ ናቸው  ብሏል ።በጭልጋ  ወረዳ  በአራት ቀበሌዎች ውስጥ ቤቶችን በማቃጠልና ዘረፋ በማድረግ የተጀመረው  ግጭት በአካባቢው ውጥረት እንዲነግስ በማድረጉም በአሁኑ ጊዜ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት  ህብረተሰቡን  የማረጋጋት ሥራ  እየተሠራ  መሆኑን  መግለጫው ጠቁሟል ።ግጭቱ  አብሮ በኖረውና በተጋመደው የአማራና ቅማንት ሕዝብ መካከል ክፍፍል  እንዲፈጠር  በሚሹ ኃይሎች ቀስቃሽነት መፈጠሩንና  በድርጊቱ  የተሳተፉ  ተዋናዮች  በቁጥጥር  ሥር  መዋል መጀመሩን  የክልሉ መንግሥት  ባወጣው መግለጫ  አመልክቷል ።    በክልሉ በየትኛውም ጊዜ በሚነሳ የማንነት ጥያቄ በአግባቡና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈታ የሚሻ መሆኑን የገለጸው  የክልሉ መንግሥት የቅማንትን ሕዝብ የማንነት ጥያቄ በመሰረቱ በመመለስ ብሄረሰቡ የራሱን አስተዳደር እንዲመሰርት መብት መሥጠቱም ይታወሳል ብሏል ።በመጨረሻም  የአማራ ክልል ሕዝብ ከመንግሥት ጎን ጋር በመቆም ፣ በልማትና እና ሰላምን  መናጋት ለማትረፍ የሚሠሩ ኃይሎችን በመታገል አንድነቱን ይበልጥ እንዲያናጠናክር ጥሪ አቅርቧል ፡፡       \nይህ ወቅት በሕዝባችን ጠንካራ ትግል እየተረጋገጠ የሚገኘውን እመርታዊ ለውጥ የምናስቀጥልበት፣ በየጉባኤዎቻችንንና ውይይቶቻችን የለየናቸውን ቁምነገሮች መሬት አስነክተን የሕዝባችንን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማስፈን የምንረባረብበት ጊዜ ነው፡፡በለውጡ ባለፉት ወራት የተከናወኑ ጉዳዮች ጅምራችን ምን ያህል ተስፋ የሚሰጥ፣ የሕዝቡን ጥያቄዎች የሚመልስ፣ የሀገራችንንም ሆነ የክልላችንን እጣ ፈንታ ብሩኅ የሚያደርግ ይታመናል፡፡ ይህንን ለውጥ ዳር በማድረስና የታለሙ ግቦችን ለመምታት በሁሉ ረገድ እየተጋን እንገኛለን፡፡ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ የሚኖሩ የአማራ ሕዝብ መብት፣ ጥቅምና ልማት ይመለከተናል ከሚሉ ወገኖች ጋር መልካም ግንኙነት በመፍጠር እያደረግን ያለው እንቅስቃሴ ተስፋ አጭሯል፡፡በሕዝቡ የሚነሱ ትክክለኛ ጥያቄዎችንም በመፍታት ለውጡ ስር እንዲሰድ ለማድረግ መጠነ ሰፊ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ሕዝባችን እየታየ ባለው ለውጥ ላይ ታላቅ ተስፋ የጣለ ሲሆን እንዳይቀለበስበትም በልዩ ልዩ አግባቦች መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡ ይሁን እንጂ በለውጡ ሒደት በየጊዜው የሚገጥሙን እንቅፋቶች ፈተና መሆናቸው አልቀረም፡፡ ይህንን ለውጥ የማይፈልጉ ሀይሎች በሚተበትቡት ሴራ የተጀመሩ መልካም ነገሮችን ለማደናቀፍ አንዳንድ እንቅስቃሴዎች አየተደረጉ እንደሆነ ይስተዋላል፡፡ የለውጡ አደናቃፊዎች ከሚጠቀሙባቸው ስልቶች መካከል ሕዝቡንና አመራሩን በልዩ ልዩ መልኩ በመከፋፈል፣ ለውጡን በማጣጣል፣ ሕዝቡ በበርካታ አጀንዳዎች እንዲጠመድና ለውጡ ፋይዳ ቢስ እንደሆነ እንዲሰማው በማድረግ ስርዓት አልበኝነት እንዲነግስ ዘርፈ ብዙ እቅስቃሴዎችን በማድረግ የሚገለጹ ናቸው፡፡ሰሞኑን በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖዎች አንዳንድ ወረዳዎችና ቀበሌዎች አካባቢ የተከሰተው ግጭትም የዚህ ማሳያ ነው፡፡ በግጭቱ ምክንያት በሕይወት፣ በአካልና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ በአካባቢውም አለመረጋጋት ተፈጥሯል፡፡ በተከሰተው ግጭት ምክንያት ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶታል፡፡ይህ ግጭት የተጀመረው በጭልጋ ወረዳ አራት ቀበሌዎች ውስጥ ቤቶችን በማቃጠልና ዘረፋ በማድረግ ነበር፡፡ ግጭቱ ከታየበት ቀን ጀምሮ አካባቢው በውጥረት ላይ ሰንብቷል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የጸጥታ ሀይሎች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመቀናጀት ሁኔታውን ለማረጋጋት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ \nየግጭቱ መንስኤ የአካባቢውን ሕዝብ አማራና ቅማንት በሚል ክፍፍል ክፍተት እንዲፈጠር፣ አብሮ በኖረው እና በተጋመደው ሕዝብ መካከል ተቃርኖ እንዲኖር በሚሰሩ ሀይሎች ቀስቃሽነት ሰዎችን በመግደል፣ ዘረፋ በማካሄድ እና ቤቶችን በማቃጠል ነው፡፡ ይህንን ግጭት ያቀናበሩና በድርጊቱ የተሳተፉ ተዋናዮችን በቁጥጥር ስር ማዋል ጀምረናል፤ ቀሪዎችንም እግር በእግር ተከታትለን ለሕግ እናቀርባቸዋለን፡፡የአማራ ብሔራዊ ክልል በውስጡ የተለያዩ ብሔረሰቦች ራሳቸውን እያስተዳደሩ በሰላም የሚኖሩበትና ማንነቶች በአግባቡ የሚስተናገዱበት እንደሆነ የሚታወቅ ሀቅ ነው፡፡ የክልሉ መንግስትም በየትኛውም ጊዜ የሚነሳ የማንነት ጥያቄ በአግባቡና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈታ የሚሻ እንደሆነ ባለፉት አመታት የነበሩ አብነቶች ምስክሮች ናቸው፡፡\nከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተነሱ የማንነት ጥያቄዎች መካከል የቅማንት ሕዝብ የማንነት ጥያቄ አንዱ ነው፡፡ ጥያቄው ከቀረበ በኋላ ህጋዊና ህገ-መንግስታዊ የሆነውን መንገድ በመከተል የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት የቅማንትን ሕዝብ የማንነት ጥያቄ በመሰረቱ በመመለስ ብሄረሰቡ የራሱን አስተዳደር እንዲመሰርት መብት ሰጦታል፡፡ የክልሉ መንግስትም የቅማንት ሕዝብ በብዛት በሚኖሩባቸው ቀበሌዎች የብሄረሰቡን አስተዳደር ለመመስረት እንቅስቃሴዎችን ጀምሯል፡፡ይሁን እንጂ የቅማንት ሕዝብ ራሱን በራሱ ለማስተዳደር ያሳየውን ፍላጎት በመጠምዘዝና የሕዝቡን የማንነት ጥያቄ በማድበስበስ \"ውሃ ቀጠነ\" በሚል የማይረባ ምክንያት የብሄረሰብ አስተዳደሩ እንዳይመሰረት ከፍተኛ ጫናና ሁከት በሚፈጥሩ ግን ደግሞ የቅማንትን ሕዝብ በማይወክሉ ሀይሎች አደናቃፊነት አስተዳደሩ ሳይመሰረት ቆይቷል፡፡ እነዚህ ሀይሎች የብሄረሰቡ የአስተዳደር ጥያቄ እንዳይመለስ የሚሰሩ፣ ለሕዝብ ተጠቃሚነት ሳይሆን ለራሳቸው ተልዕኮ መሳካት የሚንቀሳቀሱ ናቸው፡፡የክልሉ መንግስትም ችግሩን በዘላቂነት እንዲፈታና በአካባቢው በየጊዜው የሚነሱ ግጭቶች እንዲረግቡ የብሄረሰብ አስተዳደሩ ተመስርቶ ስራ እንዲጀምር ከልክ ባለፈ ትግዕስት ከሕዝቡና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይቶችን አድርጓል፡፡ ሕዝቡ የሚፈልገው በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት ተፈጥሮ፣ ከአማራ ሕዝብ ጋር እንደከዚህ ቀደሙ በአንድነትና በትብብር በመኖር የልማት ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ እንደሆነ በተደረጉ ውይይቶች ተረድተናል፡፡በሌላ በኩል ደግሞ \"የቅማንት ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ\" በሚል መጠሪያ የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛና ቅጥረኛ ቡድን በአካባቢው ረዘም ያለ አለመረጋጋትና ብጥብጥ እንዲፈጠር የሚፈልግ፣ የአማራ ብሔራዊ ክልልን ሰላምና ብልጽግና ከማይፈልጉ ሀይሎች ጋር ትስስር በመፍጠር፣ እቅድ በማውጣትና ተልዕኮ በመቀበል የእጅ አዙር መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ሰላማችንን እና ደህንነታችንን በማይፈልጉ ሀይሎች ተልዕኮ የሚንቀሳቀስ ቡድን የሕዝብ ተወካይ ሊሆን ከቶውንም አይችልም፡፡ እንዲህ አይነት ቡድን በባህሪው የራሱን ጥቅም የሚያስቀድም እንጂ ለሕዝብ ደህንነት የሚያስብ አይደለም፡፡የአማራንና የቅማንትን ሕዝብ በመለያየት ክልሉን የትርምስ ማዕከል ለማድረግ የተቃጣ ሴራ ነው፡፡ ይህ ቡድን ክልሉን ለማተራመስ አቅደው ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር የሎጂስቲክስ ድጋፍ እየተሰጠው፣ ምክር እየተለገሰው፣ የሌሎችን ተልዕኮ ለመፈጸም የሚንቀሳቀስ የቅማንትን ሕዝብ መነገጃ ያደረገ ሀይል ነው፡፡ \nከዚህ በመነሳት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሕግ የበላይነትን የማስከበር ዋነኛ ተግባሩን እንደሚከውን መታወቅ አለበት፡፡ ከዚህ በኋላ በማንነት ስም የሚነግድ የቅማንትን ሕዝብ የማይወክል ህገ-ወጥ ቡድን የሕዝቡን ሰላም ለማናጋት የሚንቀሳቀስ ከሆነ የክልሉ መንግስት ሕግ የማስከበር ሀላፊነቱን ያለ አንዳች ማመንታት ይወጣል፡፡\nየቅማንት ሕዝብ ከአማራ ሕዝብ ጋር አብሮ የሚኖር፣ በስነ-ልቦናም ሆነ በታሪክ ተመሳሳይነት ያለውና በማይላላ ገመድ የተሳሰረ እንደሆነ የሚታወቅ ነው፡፡ የቅማንትን ሕዝብ ከአማራ ሕዝብ እንዴት መለየት ይቻላል? አብሮ ታሪክ የሰራ፣ የጎንደርን ገናና ስልጣኔ የሚጋራ፣ በብዙ መለኪያ አንድ የሆነ ሕዝብ ነው፡፡የአማራና የቅማንት ሕዝብ ለዘመናት ተፈቃቅሮና ተጋምዶ የኖረ እንደመሆኑ በመካከሉ እየገቡ ሰላሙን ለመንሳት የሚንቀሳቀሱ ጥቂት ቡድኖችን አንቅሮ በመትፋት እንዲያጋልጣቸው እንጠይቃለን፡፡ አስተዋዩ ሕዝባችን እንዲረዳው የምንፈልገው አንድ ቁምነገር ይህንን ግጭት እያባባሱት ያሉት በግለሰብ ደረጃ የሚቆጠሩ ጥቂቶች እንጂ መላው የቅማንት ሕዝብ እንዳልሆነ፣ ድርጊቱም የቅማንትን ሕዝብ እንደማይወክል ከግንዛቤ በማስገባት እንደሁልጊው ሁሉ ሰላማዊ ግንኙነቱን በማስቀጠል አብሮ በፍቅር እና በመተሳሰብ መኖር እንደሚገባ ነው፡፡ \nየአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አሁን እየተደረገ ያለው ህገ-ወጥ ድርጊት የአማራን ክልል እንዳይረጋጋ ለማድረግ የተሸረበ ሴራ እንደሆነ ይገነዘባል፡፡ በመሆኑም መንግስት የሴራውን አንጓዎች በአግባቡ የለያቸው በመሆኑ የጀመረውን ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ አጠናክሮ በመቀጠል የተሸረቡ ሴራዎችን ያፈርሳቸዋል፡፡ሰላም በአንድ ወገን ብቻ ሊረጋገጥ የማይችል፣ ይልቁንም የሁሉንም ሕዝብ ተሳትፎ እና ርብርብ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡ ሕዝቡ በየአካበቢው ሰላሙን በመጠበቅ የተጀመረውን ለውጥ ወደ ኋላ ለመመለስ የሚታትሩ አካላትን በንቃት በመከታተል ከመንግስት ጎን እንዲቆም እንጠይቃለን፡፡ የክልሉን ሰላም ከኅብረተሰቡ ጋር ሆነው ለማረጋገጥ ለሚንቀሳቀሱ የጸጥታ አካላት የተለመደ መልካም ትብብር በማድረግ፣ ወንጀለኞችን በማጋላጥ በጋራ ሆነን የጀመርነውን ለውጥ ወደፊት እንድናስቀጥል ጥሪ እናቀርባለን፡፡ \nየክልሉ መንግስት ባለፉት ጊዚያት ቃል የገባቸውን ተግባራት ወደ መሬት አውርደን ለመስራት መላው የክልላችን ሕዝብ ከጎናችን እንዲቆም፣ በልማታችን እና ሰላማችን መናጋት ለማትረፍ የሚሰሩ ሀይሎችን በመታገል አንድነታችንን የበለጠ እንድናጠናክር ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ", "passage_id": "a235c657882dece2ce9c5c7c5967a82b" }, { "passage": "አዲስ አበባ:- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞንና በአማራ ክልል ጃዊ ወረዳ ተከስቶ የነበረው ግጭት ማህበረሰቡን ለማረጋጋት የሁለቱ ክልሎችና የፌዴራል መንግ ሥት የፀጥታ አካላት እየሰሩ መሆኑ ተገለጸ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግል ገል በለስ እና ዳንጉር አቅራቢያዎች ላይ የተከሰተው ግጭት እንዳይቀጥል የማረጋጋት እና ህዝብን ከህዝብ ጋር የማወያየት ተግባር በመፈፀሙ የአካባቢውን ሰላም ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። የጽሕፈት ቤት ኃላፊው አቶ ገለታ ሃይሌ በተለይ ለአዲስ ዘመን ትናንት እንደገለፁት፤ አማራ ክልል ጋር በመተባበር የሁለቱም ክልል አመራሮች ግጭቱ በተነሳበት አካባቢ ተገኝተው ማህበረሰቡን የማረጋጋት ሥራ እየሰሩ ይገኛሉ። የተጀመረው እንዳይቀጥል እና ወደ ፊትም ተመሳ ሳይ ጉዳት እንዳይከሰት ህዝብን የማወያየት ሥራ እየተሰራ ነው። ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተጨማሪ ከሚያዝያ 21 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል ጃዊ አካባቢም ከባድ ግጭት እንደነበር ተናግረው፤ በአካባቢው የሚገኙ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየሰሩ በመሆኑ አሁን የተሻለ መረጋጋት ተፈጥሯል። በቀጣይ ህዝቡ ግጭት ፈጣሪዎችን የማጋለጥ ሥራ ከሰራ እና ከመንግሥት ጋራ ከተባበረ በቀላሉ መቆጣጠር እንደሚቻልና አስተማማኝ ሰላም እንደሚሰፍንም አብራርተዋል። ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የምር መራ ቡድን ወደ ቦታው ማቅናቱን ጠቁመው፤ በጃዊ የደረሰው ከባድ እንደነበር በመጥቀስ፤ የጉዳቱ መጠን ወደ ፊት የሚገለፅ ይሆናል ብለዋል። ነገር ግን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሁለት ቀበሌ ህዝብ የተፈናቀለ ሲሆን፤ ዳንጉራ አካባቢ አይስካ ቀበሌ የ21 ሰው ህይወት እንደጠፋ እና 80 ሰው ጉዳት ደርሶበት ፓዊ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተሰጠው መሆ ኑን ጠቁመዋል። በአማራ ክልላዊ መንግሥት የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊው አቶ አሰማኸኝ አስረስ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት መተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ በተከሰተው ግጭት ምክንያት ጠቡ እየሰፋ ሄዶ ጉዳት ደርሷል። ሆኖም ከመጋቢት 18 ጀምሮ የመከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፖሊሲ እንዲሁም የሁለቱም ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ግጭቱ ወደ ተከሰተባቸው ቦታዎች በመሄድ ከፍተኛ ሥራ አከናውነዋል። አሁንም በመስራት ላይ ሲሆኑ፤ በአካባቢው ሰላም እና መረጋጋት ሰፍኗል ብለዋል። መረጃዎችን በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በየጊዜው በማሰራጨት ጉዳዩ እንዳይሰፋ እና መረጋጋት እንዲፈጠር ከመስራት በተጨማሪ፤ ከአካባቢው ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት በማድረግ የማረጋጋት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከሁለቱም ክልሎች የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች የሁለቱንም ክልሎች በጥልቀት በመመርመር የግጭቶቹን ሪፖርት እንዲያቀርቡ፤ በተጨማሪ ጉዳት እንዳያደርስ ባሉበት የመፍትሄ ሃሳብ አፍልቀው ችግሮችን እንዲፈቱ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ወደ አማራ ክልል ጃዊ ወረዳ አንድ ቡድን ተንቀሳቅሶ አሁንም እያጣራ መሆኑን ተናግረዋል። የፌዴራል መከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፖሊሲ እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ባደረገው የተቀናጀ ርብርብ ስጋት የለም ባይባልም ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ አካባቢዎች ወደ ሰላም እና መረጋጋት መግባታቸውንም አቶ አሰማኸኝ ተናግረዋል። ‹‹በጃዊ የተከሰተው በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በተፈጠረው ግጭት የተቆጡ ሰዎች ሊሆኑም ላይሆኑም ይችላሉ ›› ካሉ በኋላ፤ ይህንን የማጣራት ተግባር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ከሁለቱም ብሔረሰብ ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች መኖራቸውን በመጠቆም፤ ጉዳዩ አሳዛኝ እና አሳፋሪ ነው ብለዋል። የደረሰው ጉዳት መጠኑ እየተጣራ መሆኑን ገልፀው፤ መረጃው በትክክል ተጠቃሎ እንደደረሰ እንደሚገለጽ ጠቁመዋል። ከሁለቱም ክልል የፀጥታ ኃይል የተውጣጣ ኮሚቴ በጋራ እየሠራ መሆኑንም አመልክተዋል።  አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሚያዝያ  26/2011 በምህረት ሞገስ", "passage_id": "fc7af0cb3d4b21ce57c05e7a074e5b01" }, { "passage": "በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ እሑድ ጥር 26 ቀን 2011 ዓ.ም. በሦስት መስጊዶች ላይ ቃጠሎና ንብረት የማውደም ድርጊት ከተፈጸመ በኋላ፣ በአካባቢው ለሚገኙ ወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ምክክሮች ሊደረጉ መሆኑን ተገለጸ፡፡ በአጥፊዎች ላይ ደግሞ ሕጋዊ ዕርምጃ እንዲወሰድ ተጠይቋል፡፡በእስቴ ወረዳ ቀበሌ 03 ውስጥ የሚገኙ ሁለት መስጊዶች ላይ ሙሉ በሙሉ ማቃጠል፣ እንዲሁም በግንባታ ላይ የነበረ ሦስተኛ መስጊድ ላይ የማፈራረስ ድርጊት በአካባቢው ወጣቶች መፈጸሙን ለማወቅ ተችሏል፡፡ጥር 26 ቀን 2011 ዓ.ም. ከቀኑ 10 ሰዓት አካባቢ የተፈጸመው ይህ ድርጊት፣ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ በሆኑ የአካባቢ ነዋሪዎች የሠርግ ሥነ ሥርዓት ወቅት ነው፡፡ ዳስ ለማሳመር ከማተሚያ ቤት ተቆራርጦ በመጣ የወረቀት ማስጌጫ ውስጥ አብሮ ተገኘ በተባለ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ሥዕል ጋር በተያያዘ ድርጊቱ መፈጸሙ ተገልጿል፡፡የቤተ እምነቶቹን መቃጠል እንደተሰማ ወደ ቦታው ጉዳዩን የሚያጣራ ቡድን መላኩንና ግርግሩም ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይሠራጭ የማረጋጋት ሥራ መከናወኑን፣ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ሼክ ሙሐመድ ሐሰን ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡‹‹ቡድኑ ባቀረበለን ሪፖርት መሠረት ድርጊቱ በስሜት በተነሳሱ የአካባቢው ወጣቶች መፈጸሙን ለማወቅ ችለናል፤›› ሲሉ ሼክ ሙሐመድ አክለዋል፡፡ከቤተ እምነቶቹ ማቃጠልና ማፈራረስ ባለፈም በአካባቢው የሚኖሩ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች የንግድ ተቋማት መዘረፋቸው ተገልጿል፡፡‹‹ይህ የሚያሳየን ጉዳዩ ሃይማኖታዊ አለመሆኑን ነው፡፡ የትኛውንም አማኝ አይወክልም፤›› ሲሉ ሼክ ሙሐመድ አስረድተዋል፡፡በወቅቱ ሱቅና ንግድ ተቋማት ዘረፋ ሲካሄድ በአካባቢው የነበሩ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ድርጊቱን በመቃወም ዘረፋውን ማስቆማቸውን ዋና ጸሐፊው ተናግረዋል፡፡ ድርጊቱን በፈጸሙት ላይ መንግሥት ተገቢውን ሕጋዊ ዕርምጃ እንዲወስድ ጠይቀዋል፡፡እስካሁን ድርጊቱን መፈጸማቸው የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ለመያዝ ማጣራት እየተደረገ መሆኑን፣ በዋናነት ግን ለሁለቱም ሃይማኖቶች ምዕመናን የጋራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እንደሚከናወን ለማወቅ ተችሏል፡፡ድርጊቱን በተመለከተ መግለጫ የወጣው የአማራ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔም ጉዳት ያደረሱትን አካላት አውግዟል፡፡ የጉባዔው ተወካይና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ዋና ጸሐፊ መላከ ብርሃን ፍሰሐ ጥላሁን በበኩላቸው፣ ድርጊቱን ቤተ ክርስቲያኑ አጥብቃ እንደምታወግዝ ገልጸዋል፡፡ ‹‹የፈረሰውን መስጊድ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር በመሆን አብረን እንሠራዋለን፡፡ ድርጊቱን የፈጸሙ አካላትም ተጣርተው ወደ ሕግ መቅረብ አለባቸው፤›› ብለዋል፡፡በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የከተማ ልማትና የኮንስትራክሽን አማካሪ አምባቸው መኮንን (ዶ/ር) ወደ አካባቢው በመሄድ የሙስሊሙን ማኅበረሰብና ሌሎች ነዋሪዎችን አነጋግረዋል፡፡ ጉዳት የደረሰባቸውን ጭምር በማፅናናት፣ አጥፊዎች ለሕግ መቅረብ እንዳለባቸውና መስጊዶችም በትብብር በተቻለ ፍጥነት እንዲገነቡ መመቻቸት እንዳለበት መናገራቸው ታውቋል፡፡የአማራ ክልል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ የሱፍ ማሩ፣ በመስጊዶቹ ላይ የተፈጸመው ድርጊት ሰላም የማይፈልጉ ኃይሎች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መልካም እሴቶች በነበሩበት እንዲቀጥሉ የእምነት ተቋማትና መሪዎች ምዕመኖቻቸው ከእንዲህ ዓይነት ድርጊት እንዲቆጠቡ ማስተማር እንዳለባቸው፣ በኅብረተሰቡ ውስጥ ሰላም የማይፈልጉ ኃይሎች የፈጠሩት ሴራ ስለሆነ መንግሥት አስፈላጊውን የሕግ ዕርምጃ እንዲወስድ ጠይቀዋል፡፡", "passage_id": "d980ab0f9c0dc09134bd7b64592ec535" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ህዳር 30፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል 130 የቅማንት የማንነት ኮሚቴ አባላት የተደረገላቸውን የሰላም ጥሪ ተቀበለው በመግባት በአካባቢው ሠላም ዙሪያ እየመከሩ መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ይርሳው በክልሉ ሰላም፣ ደህንነት እና እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ዙሪያ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።አቶ ጌትነት በመግለጫቸው በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች ተከስተው የነበሩ ግጭቶችን ለመፍታት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል።በዚህም ከቅማንት የማንነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን ግጭት ከመከላከያ ሰራዊት፣ ከክልሉ ልዩ ሃይልና ከማህብርሰቡ ጋር በመሆን በውይይት መፍታት መቻሉን አስረድተዋል።የክልሉ መንግስት ለቅማንት የማንነት ኮሚቴ ባደረገው ጥሪ መሰረት 130 የቅማንት ኮሚቴ አባላት ጥሪውን ተቀብለው በመግባት በአካባቢው ሠላም እና ደህንነት ዙሪያ ከመንግስት ጋር እየመከሩ መሆኑን ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት።በተመሳሳይ በሰሜን ሸዋ እና በኦሮም ብሄርሰብ አስተዳደር አካባቢ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት በውይይትና በዕርቀ ሰላም መፈታቱን አንስተዋል።ከቤኒሻንጉል ጉምዝ እና ከአፋር ክልሎች አጎራባች ወረዳዎች ጋር ውይይት በማድረግ ከአማራ ክልል ውጭ የሚኖሩ የክልሉ ተወላጆች በሰላም እንዲኖሩ መደረጉንም ጠቁመዋል።በሌላ በኩል ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ የግብርና ሠብል ምርቱን እንዳያበላሽ ለመከላከል በክልሉ ከታረሰው 4 ነጥብ 39 ሚሊየን ሄክታር መሬት ውስጥ 2 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት ሰብል ወይም 45 በመቶ መሠብሠቡን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።በቀጣይ ሰብሎችን በተገቢው ሰዓትና ጊዜ የመሰብሰብ ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ተናግረዋል።በጣና ሃይቅ ላይ የተከሠተውን የእምቦጭ አረም ለማስወገድም የተለያዩ የመከላከያ ዘዴዎችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።በዚህ መሰረትም በአሁኑ ወቅት በሰው እና አራት ማሽነሪዎችን በመጠቀም የመከላከል ስራ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ጌትነት፥ በቀጣይ በስነ-ህይወት እና በኬሚካል ዘዴዎች አረሙን የመከላከል ስራ ይሰራል ብለዋል።የክልሉን ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትኩረትና በቅንጅት የሚሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል።በናትናኤል ጥጋቡ", "passage_id": "def753bfef87acb34a0e385000641dbe" } ]
2b565e886bd47c4f1e6fd060e416f66e
cd6a57d313eac221797467ea6105f782
በሃይማኖታዊ በዓላት ወቅትና በአገልግሎት መስጫዎች የኮቪድ-19 መመሪያዎች እንዲተገበሩ ተጠየቀ
በኃይሉ አበራአዲስ አበባ:- በሃይማኖት ተቋማትና በሁሉም አገልግሎት መስጫዎች የኮቪድ-19 መመሪያ ተግባራዊ እንዲደረግ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር በጋራ ባወጡት መግለጫ ጠየቁ። በተለይ በመጪው ሳምንታት የሕዝብ መሰብሰብን የሚፈልጉ ሃይማኖታዊ በዓላት ወቅት የኮቪድ-19 ይበልጥ እንዳይስፋፋ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራዎች በብዙኃን መገናኛ በኩል እንዲሰሩም ተጠይቀዋል።የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ በመግለጫቸው ወቅት እንዳሳሰቡት፤ የኮቪድ -19 በዓለማችን ከተከሰተ አንድ ዓመት መሆኑን እና በቅርብ ጊዜም ባህሪውን ቀይሮ በመምጣቱ የዓለም ሀገራት ዳግም ገደቦችን እየጣሉ ይገኛሉ። በኢትዮጵያም የብዙዎችን ሕይወት መቅጠፉን እና ዛሬም ቢሆን ተጨባጭ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን መዘንጋት አይገባም በመሆኑም በሁሉም የሃይማኖት ተቋማት የሚገኙ አማኞች የተቋማቸውን የኮቪድ-19 መመሪያ በምልዓት ሊተገብሩት ያስፈልጋል። ይህ እንዲሆን ደግሞ መመሪያዎችን አስመልክቶ በየቤተ ዕምነቱ የሚገኙ የሃይማኖት አባቶችና ሁሉም አማኞች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው የተጠቆሞ ሲሆን፤ በቀጣይ ሳምንታት እና ቀናት በክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ ተከታታይ ሃይማኖታዊ በዓላት የሚከበርበት ወቅት ከመሆኑ አንጻር የቫይረሱ ስርጭት እንዳይባባስ ሁሉም የበዓሉ አክባሪዎች ተገቢውን የጥንቃቄ እርምጃ እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ጉባኤ በአጽንኦት አሳስቧል።የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ በበኩላቸው፤ የኮቪድ 19 መመሪያ ቁጥር 30 ካስቀመጣቸው ድንጋጌዎች አንዱ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ፣ እጅን በውሃና ሳሙና መታጠብ፣ የፊት ማስክ በትክክለኛው ማድረግ ሲሆኑ፤ እነዚህን የመመሪያውን ግዴታዎች መተግበር የሁሉም ማህበረሰብ ኃላፊነትእንደሆነ አሳስበዋል። የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትም «ማስክ ከሌለ አገልግሎት የለም» የሚለውን መርህ ተግባራዊ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።በሀገራችን እስካሁን ድረስ የአንድ ሺህ 882 ሰዎችን ሕይወት ያጣን መሆኑን አስታውሰው ቀጣይ ጊዜ የተሻለ እንዲሆን በመመኘት በተለይ እንደ ቁልቢ ገብርኤል ባሉ በዓላት ብዙ ሰዎች በሚሰባሰቡባቸው ቦታዎች አካላዊ ርቀት እንዲጠበቅ፣ የአፍና የአፍንጫ ጭንብል ማድረግ አስገዳጅ እንዲሆኑ፣ እጅን በውሃና በሳሙና መታጠብ ካልሆነም ሳኒታይዘር እና አልኮል በመጠቀም አስፈላጊ ጥንቃቄዎች ሊደረጉ እንደሚገባ አሳስበዋል።እነዚህን መመሪያዎች ተግባራዊ ማድረግ ከተቻለ የቫይረሱን ስርጭት እና ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ መቀነስ እንደሚቻል የዓለም ተሞክሮ እንደሚያሳይ በመጠቆምም፤ በኮቪድ-19 መመሪያዎች ተግባራዊነት ላይ ከበጎፍቃደኞች፣ ከሴቶችና ወጣት አደረጃጀቶች እንዲሁም ከብዙኃን መገናኛዎች ጋር በስፋት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።በቀጣይ ስድስት ወራት የተለያዩ አካላት በሚሳተፉበት የዘመቻ መርሃ ግብር በጉራማይሌም ቢሆን በአዲስ አበባ ብቻ የሚስተዋለው የፊት ማስክ አጠቃቀም በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በትክክል ተግባራዊ እንዲደረግ፣ እጅን በውሃና በሳሙና መታጠብ ወይም ሳኒታይዘር ማጽዳት እንዲሁም አካላዊ ርቀትን የመጠበቅ ሥርዓቶችን የማጠናከር ሥራዎች ይሰራሉ ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38246
[ { "passage": "የዓለም ስጋት የሆነውና በርካቶችን እያጠቃ ያለው የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ ከተገኘ በኋላ መንግስት እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል፡፡ በቅድሚያም ነጋዴዎች የዋጋ ንረት እንዳያስከትሉ፣ ህዝቡ ንጽህናውን እንዲጠብቅና ርቀቱን ጠብቆ እንዲንቀሳቀስም መመሪያዎች እየተላለፉ ነው፡፡\nቫይረሱ በአንድ ጃፓናዊ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ከተገኘበት መጋቢት 4 ቀን ጀምሮም በበርካታ ነጋዴዎች ላይ እርምጃዎች ተወስደዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባስተላለፉት መመሪያ መሰረትም ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል፣ስፖርታዊ ውድድሮችም ተቋርጠዋል፡፡ ይሁንና እርሳቸው በፕሬዝዳንትነት የሚመሩትን ብልጽግና ፓርቲን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት ግን በተለያዩ አካባቢዎች ስብሰባዎችን ሲያደርጉ ተስተውሏል፡፡\nበዚህም መሰረት በአማራ ክልል ምስራቅ እና ምዕራብ ጎጃም ዞኖች፣ በደቡብ ወሎ ዞን፣በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፣ ብልጽግና ፓርቲ ስብሰባዎች ተደርገዋል፡፡\nቅርንጫፍ ለመክፈት በሚል የወሎ ዩኒቨርሲቲ ከሰሞኑ በከሚሴ ከተማ ያደረገው ስብሰባም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ መመሪያ በኋላ የተካሄደ ነው፡፡\nየህክምና ባለሙያዎች ቫይረሱን ለመከላከል ርቀትን መጠበቅ እንደሚበጅ ቢመክሩም ስብሰባዎቹ ግን አሁንም አልቆሙም፤መካሄዳቸውም ቀጥሏል፡፡\nበክልሉ በመካሄድ ላይ ስላሉት ስብሰባዎች የጠየቅናቸው አንድ የአማራ ክልል ብልጽግና ጽ/ቤት ከፍተኛ አመራር እየተካሄደ ያለው ስብሰባ ሳይሆን ለአመራሮች መመሪያ የማስተላለፊያ መንገድ ነው ብለዋል፡፡ “ስብሰባ ነው እየተካሄደ ያለው የሚለው ውሸት ነው” ሲሉም ነው የገለጹት፡፡\nየፓርቲው የውጭና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አወሉ አብዲም ይህንኑ ሃሳብ ይጋራሉ፡፡\n“እየተካሄደ ያለው ስብሰባ አይደለም፣ይልቁንም እየተስፋፋ ያለውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት መሰረት በማድረግ አመራሩ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ ለማድረግ እንደሚያስችል የታመነበት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው” ሲሉም ነው የሚያስቀምጡት፡፡\nወረርሽኙን ለመከላከል የአመራሩ ሚና ምን መሆን እንዳለበት ለማስገንዘብ በማሰብ የሚካሄድ ነው የተባለለት ይህ መድረክ ለወረርሽኙ አያጋልጥም ወይ በሚል የተጠየቁት ኃላፊው “የጤና ባለሙያዎች ምክረ ሃሳብ እንዲሰጡ እየተደረገ ነው” በሚል መልሰዋል፡፡\n“በአንድ ክፍል ውስጥ ከ10-20 ሰዎች ብቻ እንዲገኙ በማድረግ ርቀትን ጠብቆ (ሶሻል ዲስታንስ)” በመካሄድ ላይ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡\nየአካባቢንና የግል ንጽህናን የመጠበቅ ዘመቻዎችም አሉ ብለዋል አቶ አወሉ፡፡\nእነዚህ ስብሰባዎች እስከ መቼ ይቆያሉ በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ገና ያልተጀመረባቸው ቦታዎች መኖራቸውን የገለጹ ሲሆን እንደክልሎች ነባራዊ ሁኔታ እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡ስ ብሰባውን ገና አልጀመረም በሚልም አዲስ አበባን በማሳያነት ጠቅሰዋል፡፡\nየፓርቲው የስራ ሃላፊዎች ይህንን ይበሉ እንጅ በተለያዩ አካባቢዎች የተደረጉት ስብሰባዎች ርቀትን ያልጠበቁና በጣም መጠጋጋት ያለባቸው ናቸው በሚል በማህበራዊ የትስስር ገጾች ጭምር በመተቸት ላይ ይገኛሉ፡፡ የቫይረሱን ስርጭት ይበልጥ ሊያባብሰው እንደሚችልም ነው የሚጠቀሰው፡፡\nከዛሬ ጀምሮም በደቡብ ክልል ጌዲዮ ዞን የብልጽግና ፓርቲ አባላት ስብሰባ ሊያደርጉ እንደሆነ ተሰምቷል፡፡\n", "passage_id": "ee4cb6a358acd07fe402b22e856d72b7" }, { "passage": "ኮሚሽኑ እንዳለው የወረርሽኙ ስጋት ባለበት ሁኔታ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች መልሰው እንዲጀመሩ ለማድረግ በተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።\n\nየአገሪቱ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት አቶ ኤሊያስ ሽኩር እንደተናገሩት በበሽታው ምክንያት የተቋረጡትን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ከዚህ በላይ እንዲዘገዩ ማድረግ በስፖርት ቤተሰቡ ላይ የሚፈጠረው ጫና ከፍተኛ ነው ብለዋል። \n\nየኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰትን ተከትሎ የበሽታውን መስፋፋት ለመቆጣጠር ሲባል በአገሪቱ ስፖርታዊ ስልጠናዎች፣ ውድድሮች በአጠቃላይ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ተደርጎ ቆይቷል።\n\nበዚህም ሳቢያ የስፖርት ዘርፍ ክፉኛ መጎዳቱን ያመለከተው ኮሚሽኑ፤ ክለቦች የመፍረስ አዳጋ እንደተጋረጠባቸውና የስፖርት ቤተሰቡም የሥነ ልቦና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ መግባታቸውን ገልጿል። \n\nበመሆኑም አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ የስፖርት እንቅስቃሴዎችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችንና የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ መሠረት በማድረግ ረቂቅ መመሪያው ተዘጋጅቶ ውይይት ተካሂዷል።\n\nመመሪያው አጠቃላይ የስፖርት እንቅስቃሴዎች በምን ሁኔታ መከናወን እንዳለባቸው የሚያሳይ ሲሆን የስፖርት ተቋማትና ማኅበራት ከሚያካሂዷቸው ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ባህሪ አንጻር አስፈላጊ የጥንቃቄና የአሠራር ሥርዓት ሊያዘጋጁ እንደሚችሉ እንደሚያመለክት ኮሚሽኑ ገልጿል። \n\nበዚህም መሰረት የስልጠናና የውድድር ስፍራዎች ለበሽታው ያላቸውን ተጋላጭነት ባገናዘበ ሁኔታ ደረጃ በደረጃ በግልና በቡድን አነስተኛ ተሳታፊ ቁጥርን ታሳቢ ያደረገ ሊሆን እንደሚገባ ተቀምጧል። \n\nእንዲሁም ወደ ስልጠናና ወድድር የሚገቡ አካላት ምርመራ ማድረግ፣ የንጽህና መጠበቂያዎችን መጠቀምና ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚያገለግሉ ቦታዎች፣ ቁሳቁሶችና መሳሪያዎች ንጽህናቸው ሊጠበቅ እንደሚገባ መመሪያው ጠቅሷል። \n\nባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የእግር ኳስ ውድድርን መልሶ ለማስጀመር እየታሰበ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ውድድሩ ሲጀመር የተመልካቹንና የስፖርተኞቹን ጤና ደኅንነት ያስጠበቀ እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎችን ለማከናወን ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል። \n\nየኮሮናቫይረስ ኢትዮጵያ ውስጥ መገኘቱ ከታወቀ በኋላ ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑና በርካታ ሰው የሚታደምባቸው ስፖርታዊ ውድድሮችን የመሰሉ እንቅስቃሴዎች እንዳይካሄዱ መደረጉ ይታወሳል። \n\n ", "passage_id": "366ae60f019c2f68ce5212abe333968c" }, { "passage": "የኢትዮጰያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳሳቢውን የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመግታትና ዋንኛ ተጠቂ የሆኑ ዜጎችን ከአደጋ ለመጠበቅ ሲባል፤ ዜጎች በመጦርያና ማገገምያ ማዕከላት ውስጥ የሚገኙ አረጋዊያንን በአካል ሄደው ከመጠየቅ እንዲቆጠቡ አሳሰበ፡፡ተቋሙ መስከረም 30/2013 ዓ. ም. ባወጣው ዘለግ ያለ ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ከዚህ ዕለት በኋላ ተግባራዊ የሚደረጉ ልዩ ልዩ መመርያዎችን በዝርዝር አስተላልፏል፡፡ ኮቪድ-19 ከተከሰተ ወዲህ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል አቋቁሞ መጠነ ሰፊ ሥራዎችን እየሠራ የሚገኘው ተቋሙ፤ ወረርሽኙን ለመከላከልና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ ስለሚወሰዱ ክልከላዎች እና ግዴታዎች በሕግ መወሰን አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው መመሪያዎቹን ያወጣሁት ብሏል።በመመርያው መሠረት፤ ማንኛውም ሰው የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርግ መንቀሳቀስ የከለከለ ሲሆን፤ ከዚህ ክልከላ ነጻ የሆኑት ዕድሜያቸው ከስድስት ዓመት በታች ያሉ ህጻናት እና በማስረጃ የተረጋገጠ የመተንፈሻ አካላት ችግር ያለባቸው ዜጎች ብቻ ናቸው፡፡አገልግሎት ሰጪዎችን በተመለከተ፤ ማንኛውም መንግሥታዊ የሆነና መንግሥታዊ ያልሆነ የግል ተቋም ሠራተኞች ከሁለት የአዋቂ እርምጃ በታች ተጠጋግተው እና የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ በጥብቅ ደንግጓል፡፡ይህም ብቻም ሳይሆን የንግድ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ላላደረገ ሰው አገልግሎት መስጠትን ክልክል አድርጓል፡፡የግልና የመንግሥት የትምህርት ተቋማትም በአካል ተቀራርቦ ትምህርት መስጠት መጀመር እንዳለበት ይፋ ሳይደረግ ማንኛውንም ተማሪ ማስተናገድ እንደሌለባቸው ተወስቷል፡፡በተለይም የህጻናት ማቆያ ማዕከሎች አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል ሳይወሰንና አገልግሎት የሚሰጥበት ሁኔታ በተመለከተ በመመሪያ ሳይወጣ አገልግሎት መስጠት አይችሉም።የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች በሕግ ከተወሰነው የመጫን አቅም በላይ ሰዎችን መጫን አይችሉም ይላል መመርያው፡፡በተለይ ደግሞ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ያላደረጉ ሰዎችን አገልግሎት መስጠት የለባቸውም ብሏል፡፡የግንባታ ፕሮጀክት አሠሪዎች በተመለከተ፤ በግንባታ ቦታዎች ላይ አስፈላጊውን ንጽህና ለመጠበቅ የሚረዱ ግብአቶች ሳይሟሉ ሠራተኞችን ማሠራት ክልክል እንደሆነ በመግለጫው አሳስቧል፡፡መመርያው ሃይማኖታዊ እና የአደባባይ በዓላት አከባበርን በተመለከተ እንዲሁም የጭፈራ፣ ሲኒማ፣ ቴአትር እና የሥዕል ጋላሪ ቤቶች በምን መንገድ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው እንዲሁም ተግባራዊ ማድረግ ስለሚገባቸው ቅድመ ጥንቃቄዎች በዝርዝር አስቀምጧል፡፡የወረርሽኙ ስርጭት ያለበት ሁኔታ በየጊዜው እየታየ ሌላ መመሪያ እስኪወጣ ድረስ የአረጋዊያን የመጦሪያ ስፍራዎች እና የማገገሚያ ማዕከላት ውስጥ የሚገኙ ሰዎችን በአካል መጠየቅ በጥብቅ የከለከለ ሲሆን፤ በመመሪያ የተደነገጉ ክልከላዎችን እና ግዴታዎችን የተላለፈ ማንኛውም ሰው አግባብነት ባለው የወንጀል ሕግ መሰረት ተጠያቂ ይሆናል ተብሏል። ይህ መመርያው ተግባራዊ የሆነው ከመስከረም 25/2013 ዓ. ም. ጀምሮ ነው፡፡", "passage_id": "d7b042f20480b6e6a82be083094a1507" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 9 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ኢትዮጵያውያን እና በኢትዮጵያ የሚገኙ ሁሉ ለአፍታም ሳይዘናጉ በኮሮና ቫይረስ ዙሪያ የወጡትን መመሪያዎች እንዲተገብሩ አሳሰቡ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፌስ ቡክ ገፃቸው ላይ ባስተላፉት መልዕክት ቫይረሱን ለመከላከል ልንወስዳቸው የሚገቡ ርምጃዎች አካላዊ ርቀትን መጠበቅ፣ እጆችን ቶሎ ቶሎ በመታጠብ በንጽሕና መያዝ፣ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብልን በአግባቡ መጠቀም እና ለተወሰነ ጊዜ በቤት የሚቆይበትን ደንብ ተግባራዊ ማድረግን ይጨምራል ብለዋል፡፡በከፍተኛ ሁኔታ በቫይረሱ ከተጠቁት ሀገራት ውስጥ አብዛኛዎቹ ያደጉ ሀገራት መሆናቸውን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እነዚህ ሀገራትም በፍጥነት እርምጃ ባለመውሰዳቸው እና የቫይረሱን ሥርጭት ለመግታት ፖሊሲዎችን ተግባራዊ ባለማድረጋቸው እንደተፀፀቱና ይህ ለኢትዮጵያም ትልቅ ትምህርት እንደሚሆን አመልክተዋል፡፡አካላዊ ርቀት እና በሙሉ ወይም በከፊል ሕዝቡ በቤት እንዲቆይ የማድረግ እርምጃ የቫይረሱ ሥርጭት በአስከፊ ሁኔታ ሳይባባስ ተግባራዊ ከተደረገ፣ ሀገራት የቫይረሱን ሥርጭት ለመግታት እና በጤና አገልግሎት ሥርዓት ላይ የሚደርሰውን ጫና ለመቀነስ ይቻላሉ ብለዋል፡፡ይህ ርምጃ ኢኮኖሚን እንደሚጎዳ ቢታወቅም፣ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ ሥርጭቱን ለመቀልበስ እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ፡፡በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኮቪድ-19 ተጠቂ ከተገኘ ጀምሮ እስካሁን 317 ሰዎች በቫይረሱ መጠቃታቸውን ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሌሎች ሀገራት ጋር ሲነጻጸር ቁጥሩ አነስተኛ ቢሆንም፥ ቀስ በቀስ እያሻቀበ ይገኛል ብለዋል፡፡የቫይረሱ በሀገራችን መገኘት በታወቀበት ሰሞን የሕዝቡ ምላሽ አዎንታዊና ቫይረሱን ለመከላከል የሚረዳ ነበር ነውያሉት፡፡መሠረት የሌላቸው መላምቶችም እየተሠነዘሩ በመምጣታቸው በርካታ ሰዎች የቫይረሱን ሥርጭት ለመከላከል የሚያስችሉ አካላዊ ርቀት መጠበቅንና እጆችን አዘውትሮ መታጠብን የመሰሉ ተግባራትን ቸል እንዲል ማድረጉን ገልጸዋል በመልዕክታቸው።እንዲሁም ብዙ ዜጎቻቸው ሕይወት በቫይረሱ ከተቀጠፈባቸው፣ የጤና አገልግሎት ዘርፋቸው ከተናጋባቸው እና ኢኮኖሚያቸው በከፍተኛ ሁኔታ ከተቃወሰባቸው ሀገራት ስሕተት ለመማር ካልቻልን የምንከፍለው ዋጋ እጅግ አስከፊ ነው ሲሉም አሳስበዋል፡፡የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "4ac3c6b03e8d29a95e9710bdd7bad481" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣መጋቢት 17፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመስተዳድር ምክር ቤት የኮረና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።ምክር ቤቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፥ ሁሉም የመንግስት ተቋማት ለአካል ጉዳተኛ፣ ዕድሜያቸው 50 ዓመትና በላይ ለሆኑ፣ ለነፍሰ ጡርና አጥቢ እናቶች፣ ከቫይረሱ ጋር ተዳብለው ጉዳት የሚያስከትል ህመም ላለባቸው ሰራተኞች እንዲሁም በየመኖሪያቸው ገጠር ሆኖ ከተማ ባለ የመንግስት ተቋም ለሚሰሩ ሰራተኞች ፍቃድ በመስጠት ቤታቸው እንዲቆዩ ማድረግ እንዳለባቸው አስታውቋል።በክልሉ ማንኛውንም አይነት ስብሰባዎችን ማካሄድ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን የገለጸው ምክር ቤቱ፥ አስቸኳይ እና የማይቀየሩ ስብሰባዎች ሲያጋጥሙ የተሰብሳቢዎችን ቁጥር ከ15 ያልበለጠ ሆኖ ተሳታፊዎች በየአንድ ሜትር ርቀት እንዲቀመጡ አሳስቧል።ከዚህ ባለፈም ህዝብ በብዛት የሚሰበሰብባቸው እና የሚጠቀምባቸው መጠጥ ቤቶች፣ የምሸት ጭፈራ ቤቶች እና ሌሎች ተመሳሳይ አገልግሎት መስጫ ድርጅቶችን ከፍቶ አገልግሎቱን መስጠት የተከለከለ መሆኑን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በሁሉም መንግስትና የግል የጤና ተቋማት ተኝተው ለሚታከሙ ህሙማን ከአንድ በላይ አስታማሚ ማስገባት፣ የስፖርት ውድድሮች፣ የአካል ብቃት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ መዋኛ ቦታዎች እንዲሁም ሌሎች የተለያዩ የመዝናኛ እና የመጫወቻ ስፍራዎችን ከፍቶ አገልግሎት መስጠትም ሆነ መጠቀም መከልከሉ ተገልጿል።በተለያዩ የእምነት ተግባራት ማከናወኛ ስፍራዎች በተለመደው መልኩ በጋራ በመሰብሰብና በመጠጋጋት የአምልኮ ስነ ስርዓት ማከናወን በከፍተኛ ደረጃ ለቫይረሱ መያዝና መሰራጨት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር በመሆኑ የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት በሀገር አቀፍ ደረጃ ያስቀመጡትን አቅጣጫዎች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባም ተመላክቷል።በሀገር እና በህዝብ ላይ የተደቀነ ግልጽ አደጋን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በማንኛውም የፋብሪካ እና የግብርና ምርቶች የዋጋ ጭማሪ ማድረግም ሆነ መደበቅ የህዝባችንን በችግር ጊዜ የመረዳዳት እሴት የሚፃረርና አስነዋሪ ተግባር ከመሆኑ በተጨማሪ በህግ የሚያስቀጣ የወንጀል ድርጊት መሆኑንም አስገንዝቧል።ከተለያዩ የአለም ሀገራት ወደ ክልሉ ለጉብኝት ወይም ለሌላ ጉዳይ በሚመጡ የውጭ ዜጎች ላይ ማናቸውም አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት መፈፀም በጥብቅ የተከለከለና የሚያስጠይቅ የወንጀል ተግባር መሆኑን መገንዘብ እና መቆጠብ እንደሚገባ አሳስቧል።በክልል ደረጃ የኮረና ቫይረስን ለመከላከልና ህዝባችንን ለመታደግ በሚደረገው ርብርብ የገንዘብ፣ የቁሳቁስ እና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ አካላትና ግለሰቦች በክልል ደረጃ በሚቋቋመው የሀብት አፈላላጊ ኮሚቴ በኩል ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።", "passage_id": "973dd9111a38de7002ef2a97e92bc173" } ]
dfc81eb41c40e28caaea6ac1cdb8b0ff
ae48c4b0103e62173970cd4e1c8d2ca8
«የትግራይን ሕዝብ እንደማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ እንጂ እንዲጎዳ በማሰብ የሚሰራ ሥራ የለም» – አቶ ዛድግ አብርሃ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ማዕከል ግንባታ ሚኒስትር
እፀገነት አክሊሉ አዲስ አበባ፦ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ እንደማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ እንጂ ሆን ተብሎ እንዲጎዳ የተሰራም ሆነ የሚሰራ ሥራ አለመኖሩን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ማዕከል ግንባታ ሚኒስትር አስታወቁ፡፡ ሚኒሰትሩ አቶ ዛድግ አብርሃ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳሉት፣ መንግሥት የሰሜን ዕዝ መጠቃቱን ተከትሎ ራሱን ለመከላከል የወሰደው እርምጃ እንዳለ ሆኖ ወደ ጦርነት የገባበት ዋናው ምክንያት መስዋዕትነትም ተከፍሎ ቢሆን የጁንታው ቡድን እንደመያዣ የያዘውን የትግራይን ሕዝብ ነፃ ለማውጣት ነው። የትግራይ ሕዝብ ሕዝባችን እንደመሆኑ እንደማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ እንጂ እንዲጎዳ በማሰብ የሚሰራ ሥራ የለም ብለዋል አቶ ዛዲግ። እንደ አቶ ዛድግ ገለጻ ጁንታው ቡድን መንገድ፣ ድልድይ፣ አየር ማረፊያ አውድሟል፤ ተንቀሳቃሽ የገንዘብ መስጫ (ኤቲኤም) ማሽኖች ከጥቅም ውጪ እንዲሆኑ አድርጓል፤ በኢትዮ ቴሌኮም መስመሮች ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት አድርሶባቸዋል፤ ከዚህ አንጻር በክልሉ የደረሰው የመሠረተ ልማት ውድመት ከፍተኛ በመሆኑ በአንድ ጀምበር መልሶ መገንባቱም ከባድ ነው። እንደዚህ ዓይነት አቅም ቢኖረንማ ኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የመሠረተ ልማት ችግር ባልተፈጠረ ነበር ያሉት አቶ ዛድግ እውነታው ግን እንደዚያ አይደለም ፤ የፈራረሱትን ወደነበሩበት ለመመለስ ጊዜ ይወስዳል ፤ አሁንም ግን ሥራዎች እየተሰሩ ነው፤ በክልሉ የባንክ አገልግሎት ለምን አይጀመርም ተብሎ ለሚቀርበው ጥያቄም መልሱ ይኸው ነው ብለዋል። ጁንታው በስንት ዓመት በብዙ ልፋትና ጥረት የተገነባን መሠረተ ልማት በ30 ቀን ነው ያወደመው፤ በአሁኑ ወቅትም መንግሥት የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ነው፤ መንገዶች እየተጠገኑ፣ የቴሌኮም መሠረተ ልማቱም እንደገና ወደ ሥራ እንዲገባ ሰፋፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፤ የባንክ አገልግሎቱም እንደዚያው፤ ነገር ግን ሕዝቡም አክቲቪስቱም ሌላውም እንደሚፈልገው በአንድ ቀን መስራት አይቻልም፤ ይህም ቢሆን ግን መንግሥት የለጋሽ አካላትን አቅም በማንቀሳቀስ ሁሉ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል። እንደ አቶ ዛድግ ገለጻ አንዳንድ አካላት እንደሚሉት ሆን ተብሎ የትግራይን ሕዝብ ለመበደል የተሰራ ሥራ የለም፤ ይህንን ለማድረግ የሚያስብ መንግሥትም አለመኖሩን አብራርተዋል። በሌላ በኩል በመሰረተ ልማቱ ላይ የደረሰው አደጋ ከፍተኛ በመሆኑና መንግሥት ብቻውን የሚፈታው ባለመሆኑ ሕዝቡም ሌላውም አቅሙን አሟጦ እንዲጠቀም ኮማንድ ፖስቱ እና ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጥረት እያደረጉ መሆኑን አቶ ዛድግ ገልጸዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 19/2013 ዓ .ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38297
[ { "passage": "ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2012 ዓ.ም. ምሽት በፋና ቴሌቪዥን በትግርኛ ቋንቋ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር፡፡ ከተነሱት ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል ለውጡና የትግራይ ክልል ሁኔታ፣ የድምፂ ወያነና የትግራይ ቴሌቪዥን መዘጋት፣ ምርጫን በተመለከተ፣ የኤርትራ ጉዳይና የፌዴራል መንግሥት ትግራይን ሊያጠቃ ነው ስለመባሉ ይገኙበታል፡፡ በማብራሪያቸው የተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች እንደሚከተለው ተጠናቅረዋል፡፡ ለውጡና የትግራይ ክልል ሁኔታ ‹‹የትግራይ ሕዝብ የማይሳተፍበት ፖለቲካ በኢትዮጵያ ይኖራል የሚል እምነት የለኝም፡፡ ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ በአሁኑ ወቅት ሦስት ችግሮች አሉ፡፡ እነዚህ ሦስት ችግሮችን በግልጽ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ የመጀመርያው ችግር ከለውጥ ጋር የተያያዘ  ነው፡፡ አገራችን ከለውጥ ጋር በተያያዘ ፈተና ውስጥ ነው ያለችው፡፡ ፈተና ውስጥ እንደምትገኝ ሁሉም ሰው ያውቃል፡፡ በርከት ያሉ የውስጥም የውጭም ፈተናዎች አሉ፡፡ በዚህ ሰዓት የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የደቡብና ሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች ፈተና ላይ ነው ያሉት፡፡ የትግራይ ሕዝብም የራሱ ፈተናዎች አሉበት፡፡ ‹‹ፈተናዎቹ የየራሳቸው የሆነ ባህሪያዊ ምክንያት አላቸው፡፡ የሁሉንም ሕዝብ ፈተና አንድ ላይ ጠቅልለህ ልትመለከተው አትችልም፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው በለውጥ ሒደት ውስጥ ስለምንገኝ ነው፡፡ ለውጡ የራሱ የሆነ ባህሪያት አሉት ብለህ ማሰብ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ለውጥ ደግሞ በባህሪው መልካም ቢሆንም እንኳን የተወሰነ ሥቃይ አለው፡፡ ልክ እንደ የወሊድ ሒደት ለውጥም ሕመም አለው፡፡ ቢሆንም ግን ከሕመሙ በኋላ የሚኖረው ተስፋ ጥሩ ስለሆነ፣ ልክ ወላድ እናት የወሊድን ሕመም እንደምትቋቋመው እኛም እያስታመምነው ነው፡፡ በለውጥ ሒደት ውስጥ በመሆናችን የሚመጡ ችግሮችን በቅርቡ መፈታታቸው እንደማይቀር አምናለሁ፡፡ ቀስ እያሉ ሊፈቱ ይገባል ይቻላልም የሚል እምነት አለኝ፡፡ ይህን ወስደህ እንደ ቋሚ ችግር ልትመለከተው አይገባም፡፡‹‹ሁለተኛው ችግር በብልፅግናና በሕወሓት መካከል ባለው ግንኙነት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በብልፅግናና በሕወሓት መካከል ያለው ግንኙነት ልዩነት መኖሩ ገሃድ ነው፡፡ ይህን የለም ልትል አይቻልም፡፡ በፌዴራልና በክልሉ ያለው ልዩነት በትግራይ ላይ ተጨማሪ ችግር መፍጠሩ ግልጽ ነው፡፡ እንደፈለግከው ተገናኝተህ ተመካክረህ በአንድ ላይ መሥራት ካልቻልክ፣ ተጨማሪ ችግር መፈጠሩ የሚቀር አይመስለኝም፡፡ ስለሆነም በለውጥ ምክንያት ብቻ ሳይሆን በድርጅቶቹ መካከል ያለው ልዩነት ሌላ ችግር ሆኗል ተብሎ ሊወሰድና ችግሩም ሊፈታ ይገባል ቢባል ትክክል ይመስለኛል፡፡‹‹በብልፅግና በኩል ሁሉን ነገር በመረዳዳት (በመግባባት)፣ በግምገማና በመነጋገር የመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን፡፡ ሁልጊዜ ቁጭ ብለን በትዕግሥት በመነጋገር ብቻ በመካከላችን ያሉ ችግሮች ይፈታሉ የሚል እምነት አለን፡፡ በሕወሓት በኩልም ቢሆን ያለውን ልዩነት በመግባባት የመፍታት ፍላጎት ያላቸው አመራሮች እንዳሉ የማይካድ ሀቅ ነው፡፡ ሁሉንም ሰው አንድ አድርገህ ልትመለከተው አትችልም፡፡ አንዳንዶቹ ሌላ ሊፈልጉ ይችላሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ልዩነቱ በሰላማዊ መንገድ ይፈታል የሚል እምነትና ፍላጎት እንዳላቸው አስባለሁ፡፡ ‹‹ይሁን እንጂ በሕወሓት በኩል ያለውን ልዩነት በግጭት የመፍታት ፍላጎት ያላቸው ጥቂት አመራሮች መኖራቸው ለሁሉም ግልጽ መሆን አለበት፡፡ ሁሉም ሰላም ይፈልጋል፣ ሁሉም ተነጋግረን ጉዳያችንን እንጨርስ የሚል እምነት አለው ብሎ መውሰድም ተገቢ አይደለም፡፡ ስለሆነም በግሌ እኔ የትግራይ ሕዝብ ወደ ግጭትና ሁከት የሚገፋፉትን አካላት፣ እንደ ልማዱ ተው ማለት አለበት የሚል እምነት አለኝ፡፡ ይህን የማድረግ የሞራልም ይሁን የብቃት ችግር እንደሌለበት አሳምሬ አውቀዋለሁ፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ሰላም የሚፈልጉትን አመራሮች ሊደግፋቸው ይገባል፡፡ ሰላም የሚፈልጉት አመራሮች የሕዝብ ድጋፍ ካገኙ አብዛኛው ችግር ይፈታል ብዬ አምናለሁ፡፡ ይህንንም ለማድረግ የትግራይ ሕዝብ ዝግጁ መሆኑን እረዳለሁ፡፡‹‹ሦስተኛው ደግሞ በሁለቱ መሀል ያለውን ልዩነት ለማስፋት የሚፈልጉ አካላት የሚፈጥሩት ችግር ነው፡፡ ይህ የለም የሚል ግምገማ ማድረግ ተገቢ አይደለም፡፡ ስላለና ስለሚታይ፡፡ እነዚህ ሦስት ጊዜያዊ ምክንያቶች ከሚፈጥሩት ችግር ውጪ ትግራይን የመጉዳት የሚባል ሐሳብ ፈጽሞ የለም ብዬ ነው የማምነው፡፡ እንዲህ ያለ ሐሳብ ያለው ግለሰብ በመንግሥት ውስጥ ካለም በችግር ውስጥ ስላለ ሊታገዝ፣ ሊገመገምና ባህሪውን እንዲመለከት ይገባል የሚል እምነት ነው ያለኝ፡፡ ከዚህ ውጭ ያለውን የፖለቲካ ጨዋታ ግን ወስደህ ከሕዝብ ጋር ደባልቀህ ማየት ተገቢ አይደለም፡፡የድምፂ ወያኔና የትግራይ ቴሌቪዥን መዘጋት‹‹ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ ፍላጎት እንደነበረን በግልጽ በአገር ደረጃ የታየ፣ እንዲሁም ተጨባጭ ዕርምጃ የወሰድንበት ሥራ እንደሆነ ዓለም ሁሉ ያውቀዋል፡፡ ከለውጡ በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ከተወሰዱ ዕርምጃዎች አንዱ የመገናኛ ብዙኃንን ክፍት ማድረግ ነው፡፡ ለትግራይ ይሁን፣ ለኦሮሚያ ይሁን፣ ለአማራ ይሁን አሁን ላይ ያለን የመገናኛ ብዙኃን ዓይነት በአገር ደረጃ ኖሮን አያውቅም፡፡ ይህ ሁሉም ሰው የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ የትግራይ ሕዝብ የነበረው የመገናኛ ብዙኃን አማራጭ በጣም ውስን ነበር፡፡‹‹እንደሚታወቀው ከለውጡ በፊት ድምፀ ወያኔና ትግራይ ቴሌቪዥን ብቻ ነው የነበረው፡፡ በአሁኑ ወቅት ከሁለቱ በተጨማሪ በሌሎች የመገናኛ ብዙኃን ፕሮግራሞችም አማራጭ ሐሳቦች ለመግለጽ የሚያስችሉ ዕድል እንዳለ፣ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የሚታወቅ እውነታ እንደሆነ ሁላችንም ልናምን ይገባል፡፡ ይሁን እንጂ በአገራችን ያሉ መገናኛ ብዙኃን በአጠቃላይ ችግር እንዳለባቸው የታወቀ ነው፡፡ የመንግሥት ይሁን፣ የግል ይሁን፣ የሃይማኖት ይሁን በተለያየ ምክንያት ችግር አለባቸው፡፡ አንዳንዱ ከአቅም ማነስ የሚመጣ ችግር ነው ያለበት፡፡ አንዳንዱ ደግሞ የመገናኛ ብዙኃንን ሥነ ምግባር ካለመረዳት የሚመጣ ችግር ይታያል፡፡ በሌሎች ደግሞ ከክፋት የሚመጡ በርካታ ችግሮች አሉ፡፡ ሆነ ብለው የውሸት ወሬ፣ ሕዝብን ከሕዝብ ችግር ውስጥ እንዲገባ የሚሠሩ የውሸት ዜና (Fake News) እየፈጠሩ የሚሠሩ በርካታ መገናኛ ብዙኃን እንዳሉ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን ችግር ለሌሎች ክልሎች ሰጥተህ በትግራይ የለም ልትል አትችልም፡፡ የትግራይ መገናኛ ብዙኃንም ቢሆኑ ከዚህ ድክመት ነፃ አይደሉም፡፡ ይህ በአገር ደረጃ የምናየው ችግር እዚያም አለ፡፡ ‹‹ችግሩን ለፌዴራል መንግሥት ሰጥተህ ራስህን ነፃ ልታደርግ አትችልም፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከሰሞኑ በብሮድካስት ባለሥልጣን የተወሰደው ዕርምጃ ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ፣ ከተፈጠረው ሁከትና ግርግርን የማባባስ ድርሻ ስለነበራቸው ነው፡፡ ሁኔታውን በድንገት ነው የሰማነው፡፡ ኃላፊነት የሚሰማው የመገናኛ ብዙኃንም ሆነ የክልል መንግሥት ሰላም እንዲወርድና ሰው እንዳይጎዳ ነበር ከሁላችንም የሚጠበቀው፡፡ ባህላችንም እንዲህ ነበር፡፡ ነገር ግን የመገናኛ ብዙኃን ሲሠሩት የነበረው ሥራ ፈጽሞ የማይጠበቅና መልካም ያልሆነ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ዕርምጃው ጊዜያዊ ነው፡፡ ዕርምጃው የትግራይ ሕዝብ አፍ እንዳይኖረው ተብሎ ነው የተወሰደው ብሎ መውሰድ ተገቢ አልመሰለኝም፡፡ምርጫን በተመለከተ ‹‹በምርጫ አስፈላጊነት ላይ ልዩነት ያለን አይመስለኝም፡፡ ሁሉም እንደሚያውቀው ለምርጫ ቀጠሮ ይዘን እየተዘጋጀን እያለን ነው ሳናስበው የኮሮና ፈተና የመጣው፡፡ እንደሚታወቀው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምርጫ እስከሚደረግ ሥልጣን ላይ ያለው እንዲቀጥል ወስኗል፡፡ ይህ ደግሞ የሚሠራው ለብልፅግና ስለሆነ ሕወሓት መቀጠል አትችልም የሚል አልነበረም፡፡ ይህ ማለት ሕወሓት በክልልም ሆነ በፌዴራል የሕዝብ ውክልናውን ይዞ እንዲቀጥል ተወስኗል ማለት ነው፡፡ ለምን ተወሰነ? እንዴት አድርገን ይህን ውሳኔ ተቀበልን? የሚለውን ሒደት ለሁለትና ለሦስት ወራት የተመለከትነው በመሆኑ፣ ራሱን ተመልሼ ልናገር አልፈልግም፡፡ ብልፅግና ፍላጎቱ ምርጫ ማድረግ ነበር፡፡ ምርጫ ቦርድ በኮሮና ምክንያት ምርጫ ማድረግ አልችልም ጊዜ ያስፈልገኛል በማለቱና ፓርላማ በመቅረቡ፣ ፓርላማውም በመወሰኑ ሒደቱን ብልፅግናም ይሁን ሕወሓት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ተቀብሎ እንዲሠራ እጠይቃለሁ፣ እንደዚያ መሆኑም ጥሩ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ ምክንያቱም ምርጫን ከዓመት በኋላ የማድረግ ጉዳይ ሆኖ ሳለ የትግራይ ክልል መንግሥት በሚሊዮኖች የሚቆጠር በጀት መድቦ ክልላዊ ምርጫ አካሂዳለሁ ማለቱ የሚገርም ነው፡፡ በአንድ ወገን ኮሮና በትግራይ ሥጋት አልሆነም ማለት ነውን? ሰው ኮሮና አይዘውም አይገለውም ማለት ነው? ወይስ ዘመናዊ የሆኑ ሆስፒታሎችና መድኃኒቶች ስላሉን ችግር የለውም ማለት ነው? በሥነ አመክንዮ (Logically) ስትመለከተው ለመረዳት ትንሽ አስቸጋሪ ነው፡፡ ‹‹በሌላ በኩል ደግሞ የትግራይ ክልል መንግሥት ሚሊዮኖችን አውጥቶ ምርጫ ከሚያደርግ ሁለትና ሦስት የውኃ ጉድጓዶችን ለምን አይቆፍርም? በትግራይ ውኃ ምን ያህል ችግር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ወይም ደግሞ አንድ ሆስፒታል አይሠራም? ለምን አንድ ትምህርት ቤት አይሠራም ብለህ ለመጠየቅ ትገደዳለህ፡፡ የልማት ጥያቄ እያለ፣ ገንዘብ የለም እያልንና የፌዴራል መንግሥት ገንዘብ አልሰጠም እያልን ለምርጫ ግን ችግር የለብንም ሚሊዮኖች አውጥተን ልናደርገው እንችላለን የሚለው እንዴት ያለ ሐሳብ ነው ብለህ ስትመለከተው፣ ለመቀበል አስቸጋሪ ነው፡፡ ሐሳቡ ምንድነው የሚለው አይገባህም፡፡ እንደሚታወቀው ምርጫውን አንድ ዓመት ታግሰን በጋራ ማድረግ የማይቻለው ለምንድነው? ቢረዝም አንድ ዓመት ነው፡፡ ለአንድ ዓመት ብለህ ይህንን ሁሉ ገንዘብ ከማጥፋት ለምን በአገር ደረጃ ያለውን ሥርዓት አክብረህና የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ውሳኔ ወስደህ አትሠራም የሚል ጥያቄ ማንኛውም ግለሰብ ሊያስብበት ይገባል የሚል እምነት ነው ያለኝ፡፡ ‹‹በሌላ በኩል ደግሞ ሕወሓት ለሌሎች ፖለቲካዊ ድርጅቶች ከልቡ ለማስረከብ ስለሚፈልግ ነው ምርጫ ማድረግ የፈለገው? እነዚህ ጥያቄዎች በቅጡ ሊመለሱ ይገባል፡፡ ከዚያ ውጪ የፌዴራል መንግሥት በክልል ጉዳይ እጁን አስገብቶ አያውቅም፣ ወደፊትም አያደርገውም፡፡ ይህን ስል ግን የፌዴራል መንግሥት ኃላፊነቱንም አሳልፎ አይሰጥም፡፡ በሕገ መንግሥቱ ላይ ያለው የፌዴራል ሥልጣን ፌዴራል መንግሥቱ የሚያከናውነው ነው የሚሆነው፡፡ እኛ ኃላፊነታችንን አሳልፈን አንሰጥም በሌሎች ኃላፊነትም እጃችን አስገብተን የሆነ ነገር አናደርግም፡፡በኤርትራ ጉዳይ‹‹የኢትዮጵያና የኤርትራ ግንኙነት ከመራራ ጦርነት በኋላ ለሃያ ዓመታት ያህል እንቅልፍ ላይ የቆየ ነበር፡፡ ስለሆነም ከረዥም እንቅልፍ በኋላ የባነነ ግንኙነት ብለህ ልትወስደው ትችላለህ፡፡ በዚህ ወቅት መልካም የሆነ ዲፕሎማሲያዊና ሰላማዊ    ግንኙነት አለን፡፡ በኢኮኖሚውም ከተመለከትነው የስልክ ግንኙነት አለን፣ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት አለን፡፡ ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ነገሮችን በጋራ መሥራት ጀምረናል፡፡ ይህ ደግሞ ቀስ እያለ ከፍ ወዳለ ደረጃ ሊደርስ እንደሚችል አምናለሁ፡፡ ይደርሳል የሚል ተስፋም አለኝ፡፡ የኢትዮጵያና የኤርትራ ግንኙነት ከፍላጎት ተነስተህ ግንኙነቱ እንዲፋጠን መመኘት የተቀደሰ ፍላጎት ነው የሚመስለኝ፡፡ ጤና ያለው ኢትዮጵያዊ ሊያስበው የሚችል ሰናይ ፍላጎት ነው ብሎ መውሰድ ይገባል፡፡ ግን ችግሩን ሊፈቱ እየቻሉ ለሃያ ዓመታት ያህል ያልቻሉ ሰዎች፣ በሁለት ዓመት ያገኘነውን ድል ማሳነሳቸው ተገቢ አይመስለኝም፡፡   ‹‹ይህ ውጤት በሥራ ነው የመጣው፡፡ አንተ ያልቻልከውን ነገር ሌላ ሠርቶት እያየህ አሳንሰህና ምንም እንዳልተደረገ አድርገህ መናገር ተገቢ አይደለም፡፡ ሌላኛው ነጥብ ደግሞ ግንኙነቱ የሁለት አገሮች ግንኙነት እንደ መሆኑ የፌዴራል ሥልጣን መሆኑ መታወቅና ሊሰመርበት ይገባል፡፡ በአጭሩ ከግንኙነቱ የሚገኘው ማንኛውም ጥቅም ለሁለቱም ሕዝቦች፣ አገሮችና መንግሥታት እንጂ ለትግራይ ሕዝብ ብቻ አይደለም፡፡ ሁላችንም ከሰላምና ከልማት ጥቅም አለን፡፡ የንግድ ልውውጡም ይጠቅመናል የሚል እምነት ይዘህ ጉዳትም ቢኖር ሁሉንም የሚጎዳ እንጂ፣ ለይተህ ለትግራይ ልትወስደው የሚቻል አይደለም፡፡ የሆነ ሆኖ ግንኙነቱ በተቃና መስመርና ደረጃ ላይ እንዳለና እየተሻሻለ እንደሚሄድ ላረጋግጥ እወዳለሁ፡፡የፌዴራል መንግሥት ትግራይን ያጠቃል? ‹‹ማን ነው ማንን የሚያጠቃው? የፌዴራል መንግሥት የትግራይ ክልልን የሚያጠቃው ለምንድነው? ይህ የዕብዶች ንግግር ነው፡፡ ‹ከተናገረው ደጋሚው› የሚለውን የትግርኛ አባባል ያስታውሰኛል፡፡ የፌዴራል መንግሥት የትግራይ ክልል መንግሥትንም ሆነ የትግራይ ሕዝብን ሊወጋ ይችላል ብለህ ማሰብ፣ በራሱ እንዴት ያለ ሐሳብ እንደሆነ ለመረዳት ለእኔ በጣም ያስቸግረኛል፡፡ ከኤርትራ መንግሥት ጋር በመሆን ትግራይን ሊያጠቁ ነው? በመሠረቱ ውጊያ ለማድረግ የሚያስብ ማንኛውም አካል ካለ በቂ የሆነ ምክንያት ሊኖረው ይገባል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ መንግሥት ብቻ ሳይሆን ሕዝቦችም እንዲቀበሉት ያስፈልጋል፡፡ አጀንዳ ብፈጥር የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዴት ነው የሚቀበለኝ? የኢትዮጵያ ሕዝብ ለምን ብሎ ነው የትግራይ ሕዝብ ሊጠቃ ይገባል ብሎ የሚያምነው? የሚለውን ነገር ለመገምገም ፖለቲከኛ መሆን አይጠይቅም፡፡ ማንኛውም ተራ ሰው ሊረዳው ይችላል፡፡ ‹‹በአገራችን በተለይ በአሁኑ ሰዓት ጦርነት ለማካሄድ የሚያስችል ምክንያት አለ ብዬ አላምንም፡፡ ወጣ ወጣ ያሉ የፖለቲካ ጨዋታዎች እዚህም እዚያም ሊታዩ ይችላሉ፡፡ ይህን ግን እንደ በቂ ምክንያት ወስደህ ወደ ውጊያ ለመሄድ አይገባም፣ ሊሆንም አይችልም፡፡ መንግሥት ውጊያ አይፈልግም፡፡ ሕዝብም ውጊያ አይፈልግም፡፡ በዚህ ምክንያት ውጊያ አናስብም አይኖርምም፡፡ የኤርትራ መንግሥትን ከኢትዮጵያ መንግሥት በጋራ ሆነን ኢትዮጵያን እንውጋ ብሎ ሊጠራው ይችላል ብሎ ማሰብ በራሱ ኃጢያት ነው፡፡ ይህ በአገራችን ታሪክ አልታየም፣ ወደፊትም ይኖራል የሚል እምነት የለኝም፡፡‹‹በአሁኑ ወቅት የኤርትራ መንግሥት ኢትዮጵያ ከሌሎች አገሮች ጋር ያላትን አንዳንድ ችግሮች ለመፍታት የተለየ ድርሻ እየተጫወተ ነው፡፡ የኤርትራ መንግሥት ፍላጎት ኢትዮጵያ ከሌሎች ጋር ሰላም ሆና ከኤርትራም ጋር ያለው የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ሥራ ከፍ ብሎ በአንድነት እንጠቀማለን የሚል እንጂ፣ ውጊያን የኤርትራ ሕዝብና መንግሥት አይፈልግም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥትም አይፈልግም፡፡ በግሌ ይህ ክስ ከሁሉም ክሶች የከፋ ነው፡፡ የፌዴራል መንግሥት በትግራይ የሆነ ዕርምጃ እወሳዳለሁ ካለ ራሱ ያደርገዋል፡፡ ይህን ማድረግ ምን ችግር ኖሮት ነው ሌሎችን እባካችሁ ኑ በጋራ ሆነን እንዲህ እናድርግ የምንለው? እውነት ለመናገር በዚህ ወቅት የኤርትራ መንግሥት የሰላም ኃይል መሆኑ፣ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን ዓለም ያወቀው ጉዳይ ነው፡፡ የትኛውም ዓለም ብትሄድ የኤርትራ መንግሥት ለሰላምና ለልማት ነው የሚሠራው እምነት ነው ያለው፡፡››", "passage_id": "89fe86b2f0587d68504a012049e94313" }, { "passage": "በኢትዮጵያ ምርጫ ለማካሄድ ምቹ ሁኔታዎች ቢኖሩም መሰራት ያለባቸው ቀሪ ተግባራት ግን እንዳሉ ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ቆይታ ያደረጉ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች አስታወቁ፡፡ፍትሃዊና ዴሞክራሲዊ ምርጫ ለማካሄድ ምቹ ሁኔታዎች ቢኖሩም ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት ይገባቸዋል ካሉት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አንዱ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር አረጋዊ በርሔ ናቸው፡፡\n", "passage_id": "c93b31a2ef26823b451e8bf7112a2c98" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ህወሓት ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ሕግ ሲጥስ የኖረ ድርጅት መሆኑንና በአሁኑ ወቅትም ለአገር ሰላም መደፍረስ ምክንያት የሆኑ ህገወጥ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የአረና ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የመድረክ ስራ አስፈፃሚ አባል አቶ ጎይቶም ፀጋዬ አስታወቁ። የአረና ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የመድረክ ሥራ አስፈፃሚ አባል አቶ ጎይቶም ፀጋዬ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ ህወሓት ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ህግ በመጣስና የጥቂቶችን አምባገነንነት በማንገስ የኖረ ድርጅት ነው። ይህም ህዝቡ የነፃነትን አየር እንዳይተነፍስ ብሎም ከህወሓት ተቃራኒ የቆመውን ሁሉ በጠላትነት ፈርጆ እንዲሰለፍ አድርገውታል። ለዚህም በ1993 ዓ.ም በድርጅቱ የነበረው መከፋፈል ዋነኛ ማሳያ መሆኑን ያስታወሱት አቶ ጎይቶም፤ በወቅቱ የድርጅቱ ህገ ደንብ በጣሰ መልኩ ምላተ ጉባኤው ባልተሟላበት ሁኔታ ፍትሃዊነት እንዲሰፍን የተሟገቱ አባላት እንዲባረሩ መደረጉን ጠቁመዋል። « በድርጅቱ መሃል ሰፋሪ የሚባል ነገር የለም» ያሉት ምክትል ሊቀመንበሩ፤ አመራሮቹን የማይደግፍ ሁሉ በጠላትነት የሚፈረጅበት አሰራር ያለው አምባገነን አስተሳሰብ የሰፈነበት ፓርቲ መሆኑን አስገንዝበዋል። አረና ሲቋቋም ትግራይ ከሁለት ፓርቲ በላይ መሸከም አትችልም፤ ክፍፍል ያመጣል ተብሎ ከፍተኛ ተቃውሞ ደርሶባቸው እንደነበርም ተናግረዋል። «በተለይም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር በአንድ መድረክ ላይ አንድ እንስራ ከተሰነጠቀ ዳግመኛ እንደማያለግለው ሁሉ ተጨማሪ ፓርቲ መኖር በትግራይ ህዝብ መከፈፋልን የሚያመጣ በማለት ህዝቡ ፈፅሞ ሌላ አማራጭ እንዳያስብ አድርገውታል» ብለዋል። ይህ አስተሳሰብ ዛሬም ድረስ በከፍተኛ ደረጃ የተንሰራፋ ከመሆኑም በላይ ህገመንግስቱ ያስቀመጠውን በነፃነት የመተዳደር መብት የሚጥሱ ተግባራት እንደሚ ፈፀሙ ጠቁመዋል። ይህም ድርጅቱ ራሱ ያፀደቀውን ህገመንግስት እንኳ የማያከብር መሆኑን ትክክለኛ ማሳያ መሆኑን አስገንዝበዋል። እንደ አቶ ጎይቶም ማብራሪያ፤ የድርጅቱ ኢ-ፍትሃዊ አስተሳሰብ በክልሉ ነግሶ እንዲቆይ በክልሉ ያሉ ሚዲያዎች ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። በክልል ደረጃም ሆነ በትግራይ ህዝብ ስም የተቋቋሙ አብዛኞቹ ሚዲያዎች ከህወሓት አመራሮች የሚሰጣቸውን የሃሰት ሪፖርቶች ተቀብለው የፕሮፖጋንዳ ስራዎችን በህዝቡ ላይ የሚያሰርፁ ናቸው። የዜናም ሆነ የትንታኔ አቅጣጫዎቻቸው የጋዜጠኝ ነትን መርሆን ያልተከተሉና ከውግንና ያልፀዱ ከመሆና ቸውም ባሻገር፣ ህዝቡን ውዥንብር ውስጥ ከተውታል። ሚዲያዎቹ የሚያቀርቧቸው ተንታኞችና ባለሙያዎችም የህውሃትን አቋም ብቻ የሚያራምዱ ለህዝብ ጥቅም ያልቆሙ እንደሆኑም አመልክተዋል ። ሚዲያዎቹ በሌላ ብሄርና በፌዴራል መንግስት የተሰሩ ስራዎችን ህፀፅ በማውጣት ላይ የተጠመዱ መሆናቸውን አቶ ጎይቶም ጠቅሰው፣ ይህም የክልሉ መንግስት ያለበትን ክፍትት አይቶ ለህዝቡ ትክክለኛ ዴሞክራሲ እንዳያሰፍን ምክንያት መሆናቸው አስገንዝበዋል። በገለልተኛ ተቋም የተመሰረቱ የውጭና የአገር አቀፍ ሚዲያዎችም ቢሆኑ በህወሓት አመራሮች የሚደርስባቸውን ዱላና ዛቻ በመፍራት የትግራይ ህዝብ ያለበትን ጫና በገሃድ የማያወጡ መሆናቸውን አብራርተዋል። «በትግራይ ያሉና የውጭና በፌዴራል ደረጃ ያሉ ሚዲያዎችም ከህወሓት አባላት ጋር ቅርበት ከሌላቸው ምንም አይነት መረጃ የማያገኙ በመሆኑና በቤተሰባቸውና በራሳቸው ላይ ችግር የሚደርስባቸው በመሆኑ በፍፁም ሚዛናዊ ዘገባ ማካሄድ አይችሉም» በማለት ተናግረዋል። በሌላ በኩል ህወሓት በትግራይ ክልል የተቋቋሙ ፓርቲ አባላትን እያሳደደ ከመንግስት ስራ እያፈናቀለና ኢሰባዊ ድርጊት እየፈፀመ ባለበት በዚህ ወቅት ምርጫ መካሄድ አለበት ብሎ መሞገቱ ተገቢ አለመሆኑን አቶ ጎይቶም አንስተዋል። ህወሓት በክልሉ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ተቋም ሳይመሰርት እንዲሁም ለዚህ ምንም አይነት ዝግጅት ባላደረገበት ሁኔታ ምርጫ ይካሄድ ማለቱ የራሱን ችግር ለመሸፈን የሚያደርገው ግርግር እንደሆነ አቶ ጎይቶም አስረድተዋል። በዚህ ረገድ ፓርቲያቸው በትግራይ ያለው ኢ-ዴሞክራሲያዊ ተግባር እስካልቆመና ምቹ ሁኔታዎች እስካልተከናወኑ ድረስ ምርጫ መካሄድ የለበትም በማለት ለምርጫ ቦርድ በተደጋጋሚ ማመልከቱን ተናግረዋል። «ለይስሙላ የሚደረግ ምርጫም ሆነ የሚያስከፍለው ዋጋ ለህወሓትም ሆነ ለሌላውም ከፍተኛ ነው» ያሉት አቶ ጎይቶም፤ በሌላ በኩል ህገመንግስቱን በመጣስ የሚደረጉ የጉልበት እንቅስቃሴዎች ከፍተኛ ኪሳራዎች የሚያስከትሉ እንዳይሆኑ ያላቸውን ስጋት ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ህውሓት አገሪቱን ወደ ጦርነት የሚከት ተግባር ይከተላል የሚል እምነት ባይኖራቸውም ሁኔታዎች ወደእዛ እንዳያመሩ ውስጡን እንዲፈትሽ አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 10/2012ማህሌት አብዱል", "passage_id": "ab975d1c6189c614f283438c2e28e0da" }, { "passage": "በትጥቅ ትግሉ ወቅት ስለነበራቸው ሚና እንዲሁም ስለወቅታዊ የኢትዮጵያ የፖለቲካዊ ሁኔታ ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር ቆይታ አድርገዋል።\n\nቢቢሲ፡ ህወሓት ከተመሠረተበት ግዜ አንስቶ በክብር እስከተሰናበቱበት ድረስ አመራር ላይ ነበሩ። ከልምድዎ እጅግ የሚኮሩበት ወይም እንዲህ ባደርግ ኑሮ ብለው በግል ወይም እንደ ድርጅት የሚቆጩበት ነገር አለ?\n\nአቦይ ስብሃት፡ እንደ ድርጅት ድክመት አልነበረብንም አልልም፤ ብዙ ድክመቶች ነበሩብን። በግልም ስህተቶችን አልፈፀምንም አልልም። \n\nእኔም በግሌ አንዳንድ ስህተቶችን ፈጽሜያለሁ፤ ሆኖም በቅጽበት ይታረም ነበር። የሓኽፈን ውጊያ የኔ ስህተት ነበር ውጊያው ድል አልነበረም። ግን በፍጥነት ተምረን በፍጥነት ነበር የምናርመው። \n\nከድክመት እንማር ነበር፤ በድልም የመርካት ሁኔታ እንዳይኖር እንማርበት ነበር። በድል መስከር አይገባም። የኢትዮጵያ መጻኢ ታሪክ ተጽፏል፤ ፕሮግራም ላይ ሰፍሯል። ከዚሁ በመነሳት ነው 'ትግሉ ረጅምና መራራ ነው፤ ድል ግን አይቀሬ ነው' ነው የተባለው።\n\n• ህወሓት: \"እሳትና ጭድ የሆኑ ፓርቲዎች ሊዋሃዱ አይችሉም\" \n\nቢቢሲ፡ ሥልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ሥርዓቱ በሙስና በስብሷል ይሉ ነበር። እርስዎና ቤተሰብዎ ግን በሙስና ትታማላችሁ ምን አስተያየት አለዎት?\n\nአቦይ ስብሃት፡ ሙስና ቀስ እያለ የሚመጣ ችግር ነው። ሙስና አለ በሚለው ላይ 'መጠኑ ትንሽ ነው፤ አይደለም መጠነ ሰፊ ነው' የሚል ክርክር ነበር። ይብዛም ይነስም ምልክቱ ሲታይ ቶሎ መታረም ነበረበት። ኋላ ላይ እያደገ መጥቶ ሙስናን መጸየፍ እየደከመ መጣ።\n\nሙስና የሥርዓታችን ዋነኛው ጠላት ነው እየተባለም ጥንቃቄያችን ግን እየቀነሰ መጣ። በ2008 እናጽዳው ተብሎ ታወጀ። ጸረ ዴሞክራሲያዊ ጠባብ ብሔረተኝነት (ጠባብነትና ትምክህት ማለት ነው)፣ የሃይማኖት አክራሪነት ጠላቶቻችን ናቸው ብለን ለይተን አስቀመጥን። \n\nዋናው ተጠያቂ ደግሞ የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ነው፤ በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ምክትሉ ናቸው ብለን አስቀመጥን። ስለዚህ በፍጥነት መታደስ አለብን ብለን ወሰንን። ዶክተር ዐብይ ከተመረጠ በኋላም አሁንም በፍጥነትና በጥልቀት መታደስ አለብን ካልሆነ ኢትዮጵያ አደጋ ውስጥ ነው ያለችው አልን።\n\nይህ ሳይተገበር ቀረ፤ እንዴት ቀረ? ማን አስቀረው? ተአምር ነው። \n\nአንድን ነገር ሊሆን አይገባውም ካላልክ በስተቀር ይለመዳላ፤ አሁን እየተለመደ ነው። ይህ ጉዳይ እንዴት ጠፋ ስትል፤ እኔ ጠፍታ ዳናዋ ካልተገኘው የማሌዥያ አውሮፕላን ጋር ነው የማመሳስለው።\n\nቢቢሲ፡ እርስዎን በተመለከተ ሰለሚነገረውስ? \n\nአቦይ ስብሃት፡ የዚያው አካል ነው። መጣራት አለበት እሱ እንዲሆን እኮ ነው እየተጠየቀ ያለው። ሙሰኛ ማነው? አቶ እገሌ ወይስ ወይዘሮ እገሊት? ደፍሮ የሚያወጣው ነው የታጣው። ወኔ የለም፤ ድፍረት እኮ ነው የታጣው። \n\nየአገር ውስጥ ሙያተኞች ከውጭ ባለሞያዎች ጋር ሆነው እንዲሠሩ 'ፕሮፖዛል' ለአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ ደመቀ መኰንንና አቶ አባይ ወልዱ ቀርቦ ነበር። እንገባበታለን ተብሎ ቀረ።\n\nነጻና ገለልተኛ በሆነ አካል መጣራት ነበረበት። አንተስ ብትለኝ እዚያው ውስጥ መጣራት አለብኝ።\n\n• \"ለስልጣን ተብሎ የሚፈጠር ውህደትን ህወሓት ፈጽሞ አይቀበለውም\" አቶ ጌታቸው ረዳ \n\nቢቢሲ፡ አቦይ ስብሃት በአሁኑ ሰዓት ምን ዓይነት ሚናና ኃላፊነት አለዎት?\n\nአቦይ ስብሃት፡ የእኔ እምነት የህወሓት/ኢህአዴግ ፖለቲካዊ ፕሮግራም ነው። አሁን አለ ወይስ የለም የሚለውን ቆይቼ እገልጸዋለሁ። በግል የህወሓት ደጋፊ ነኝ። ትግራይ ውስጥ ትግራይን፤ ከትግራይ ደግሞ ለኢትዮጵያ፤ ህወሓትን የሚተካ የፖለቲካ ኃይል የለም።\n\nበመተዳደሪያ ሕጉ መሰረት [የህወሓት] አባል አይደለሁም። እየተናገርኩ ያለሁትም ህወሓትን... ", "passage_id": "c590b94cc04a6cf2a20fec0c67ea7d0c" }, { "passage": "በአሁኑ ጊዜ ትግራይ ውስጥ የሚካሄድ ጦርነት እንደሌለና እየተደረገ ያለው የህወሓት አመራሮችን በማደን በቁጥጥር ስር የማዋል እርምጃ እንደሆነ አቶ ዛዲግ አብረሃ ገለጹ። የዲሞክራሲ ግንባታ ሚንስትሩ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በክልሉ የተካሄደው ጦርነት ማብቃቱን ጠቁመው በዚህ ወቅት \"ጦርነት የሚባል ነገር የለም። አሁን ጥቂት የሚባሉ የአሸባሪ ቡድን አባላትን እየተከታተሉ መያዝ ነው የቀረው\" ሲሉ ገልጸዋል። መንግሥት ሕግ የማስከበር ያለው ዘመቻ የፌደራል መከላከያ ሠራዊት የክልሉን ዋና ከተማ መቀለን መቆጣጠሩን ተከትሎ ማብቃቱን ነገ ቅዳሜ አንድ ሳምንት የሚሞላው ሲሆን በመንግሥት ኃይሎች እየተፈለጉ ያሉት የህወሓት አመራሮች ግን ፍልሚያ ላይ እንደሆኑ እየተናገሩ ነው። ቀደም ሲል የህወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እንደሁም የቡድኑ ከፍተኛ አመራር አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ደግሞ ትናንት ለትግራይ ቴሌቭዥን እንደገለጹት \"ጦርነቱ አልተገባደደም። አይገባደድምም\" ብለዋል።ነገር ግን ሚኒስትሩ አቶ ዛዲግ አብረሃ እየተካሄደ ያለው ተፈላጊዎችን የመያዝ ተግባር መሆኑን አመልክተው፤ በአሁኑ ወቅት \"ህወሓት ጦርነት ማድረግ የሚያስችል ወታደራዊ ቁመና የለውም። ወታደር የለውም። ትልልቅ መሣሪያዎች የሉትም። የሕዝብ ድጋፍም የለውም\" ብለዋል።ከሳምንት በፊት በተደረጉ ውጊያዎች ዋና ዋና የትግራይ ከተሞች በፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት እጅ ውስጥ ከገቡ በኋላ የህወሓት አመራር መቀለን ጥሎ ቢወጣም ጦርነቱን እንደሚገፋበት ማስታወቁ ይታወሳል።አቶ ጌታቸው ረዳም ሠራዊቱ መቀለን መቆጣጠሩን አረጋግጠው የሚቀር ነገር እንዳለ \"መቀለ ገብተዋል። መቀለን ተቆጣጠሩ ማለት ግን አይደለም። መቀለን መቆጣጠር የሕዝብን መንፈስና ልቦና መግዛት ይጠይቃል\" ሲሉም ተደምጠዋል።የመቀለ ከተማን ለመያዝ በተካሄደ ዘመቻ ወቅት ከተዋጊዎች ውጪ ባሉ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የሚያመለክቱ መረጃዎች እየወጡ መሆናቸውን በመጥቀስ፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት \"አንድም ሰላማዊ ሰው አልተጎዳም\" ማለታቸውን በተመለከተ ቢቢሲ አቶ ዛዲግ አብረሃን ጠይቆ ነበር። በሰጡትም ምላሽ ጠቅላይ ሚንስትሩ እተካሄደ ስለነበረው ዘመቻ ትክክለኛ መረጃ እንዳላቸውና የአገሪቱ ሠራዊትና የጸጥታ አካላት በክልሉ ውስጥ በቅንጅት እንደሚሰሩ ጠቁመው \"የሕግ ማስከበር ዘመቻው ስትራቴጂ ሲወጣ አንድም ስህተት ላለመሥራት ለይቶ በማትቃት [በሰርጂካል ኦፕሬሽን] ላይ የተመሠረተ ነው። ስለዚህ በእኛ በኩል የሲቪል ጉዳትን ሙሉ በሙሉ አስወግደናል\" ብለዋል።በመንግሥት በኩል በዚህ ዘመቻ ትግራይ ውስጥ ያለው ሕዝብ እንዲጎዳ እንዳልተፈለገ ጠቅሰው ለዚህም አስፈላጊው ጥንቃቄ እንደተደረገ ተናግረዋል። \"ጸቡም የሕግ ማስከበር ዘመቻውም በህወሓት ላይ እንጂ በሕዝብ ላይ የሚካሄድ አይደለም\" ሲሉም አክለዋል።አቶ ዛዲግ በተጨማሪም፤ \"በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት አልደረሰም ስንል በእኛ በኩል እንጂ በእነሱ [በህወሓት] በኩል ማለታችን አይደለም። ሰላማዊ ሰዎችን እንደ ከለላ [ጋሻ] በመጠቀም ሕይወታቸውን ለማቆየት ሞክረዋል። በዚያ ምክንያት የመጣ ጉዳት ሊሆን ይችላል\" ሲሉም ተናግረዋል።ከዚህ አንጻር በሰላማዊ ሰዎች ላይ የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ መረጃ እንደሌላቸው የተናገሩት ሚኒስትሩ፤ ዋና ከተማዋ መቀለ በአሁኑ ጊዜ እየተረጋጋች በመምጣቷ በቀጣይ መረጃ ሊያገኙ እንደሚችሉም ጠቁመዋል።የህወሓት አመራሮች ግን በዘመቻው ሂደት ከተዋጊዎች ውጪ ባሉ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን በመግለጽ በተደጋጋሚ መንግሥትን ሲከሱ ቆይተዋል። በትግራይ ክልል ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ዕለት አንስቶ የስልክ እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ በመቆየቱ በክልሉ ውስጥ ስላለው ሁኔታ ከገለልተኛ ወገን ለማረጋገጥ አልተቻለም።ከዚሁ ጋር ተያይዞ ትግራይ ውስጥ ይሠሩ የነበሩ አራት የበጎ አድራጎት ሠራተኞች በግጭቱ ወቅት መገደላቸው ተዘግቧል።ሮይተርስ የዜና ወኪል የዲፕሎማቲክና የሰብአዊ እርዳታ ድርጅት ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በሁለት የተለያዩ የውጪ የተራድኦ ድርጅቶች ተቀጥረው ይሠሩ የነበሩ አራት ኢትዮጵያውያን የሰብአዊ እርዳታ ሠራተኞች በኢትዮጵያና በኤርትራ ድንበር አቅራቢያ ተገድለዋል።ስለዚህ ጉዳዩ የሚያውቁት ነገር እንዳለ በቢቢሲ የተጠየቁት አቶ ዛዲግ አብረሃ ፤ \"አሁን ስለዚህ ጉዳይ የማውቀው ነገር የለም። ገና መረጃው እየተጠራ ነው ያለው። የስልክ አገልግሎትን እየመለስን፣ መንገዶችን እያስተካከልን ነው ያለነው\" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።በትግራይ ክልል ውስጥ የተካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ መጠናቀቁ ከተገለጸ በኋላ መንግሥት መረጋጋት ማስፈን፣ የተጎዱ መሰረተ ልማቶችን መልሶ መገንባትና የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው በመመለስ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ እንዲቋቋሙ ማድረግ ዋነኛ ትኩረቱ ማድረጉን ገልጿል። በፌደራል መንግሥቱና የትግራይ ክልልን ሲያስተዳድር በነበረው ህወሓት መካከል ለወራት የቆየው ውዝግብ ባለፈው ዓመት ሊካሄድ የነበረው አገራዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽን ምክንያት ወደ ሌላ ጊዜ መሸጋገሩን ተከትሎ በከፍተኛ ሁኔታ መካረሩ ይታወሳል። ይህንን የፌደራል መንግሥቱን ውሳኔ ባለመቀበል በትግራይ ክልል የተካሄደው የተናጠል ምርጫ የፌደራል መንግሥቱን ተቀባይነት ካለማግኘቱ በተጨማሪ በአገሪቱ ምክር ቤቶች ሕገ ወጥ ተብሎ ውድቅ ተደርጓል። የክልሉ ባለስልጣናትም በበኩላቸው ፌደራል መንግሥቱ በኮቪድ ሰበብ ምርጫን ማራዘሙ \"ሕገመንግስቱ ከሚፈቅደው ውጭ ነው ስልጣኑን አራዝሟል\" በማለት የፌደራሉን መንግሥት \"ሕገወጥ\" ብለው እውቅና መንፈጋቸው አይዘነጋም።የፌዴሬሽን ምክር ቤትም የክልሉን አስተዳዳሪዎች ሕገ መንግሥቱን በመጣስና ከሕግ ውጪ ተንቀሳቅሰዋል በማለት የፌደራል መንግሥቱ ከትግራይ ክልል ክልል አስተዳደር ጋር የነበረውን የቀጥታ ግንኙነት አቋርጦ የበጀት ዕቀባ ጥሎ ነበር። አለመግባባቱና መካሰሱ ያለማቋረጥ በቀጠለበት ሁኔታ ጥቅም 24/2013 ዓ.ም ምሽት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በትግራይ ክልል በነበሩት የሠሜን ዕዝ አባላት ላይ በህወሓት ኃይሎች ጥቃት መፈጸሙን ይፋ ካደረጉ በኋላ የፌደራሉ ሠራዊት በህወሓት ኃይሎች ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመሩ ይታወሳል። ባለፈው ቅዳሜ የክልሉ ዋና ከተማ መቀለ በፌደራል መንግሥት ሠራዊት ቁጥጥር ሰር ከዋለች በኋላ ወታደራዊ ዘመቻው መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አሳውቀዋል። ", "passage_id": "e91fbfcad3b9bcf43a9ab6bb41673ca0" } ]
6db58fd9d51d012d763a2a984cb5970d
15ea803cc0c235f4246ab9e63d7079e1
በሀዋሳ ከተማ በ1ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር የዘይት መጭመቂያ ፋብሪካ ሊገነባ ነው
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያ የሆነው የዘይት መጭመቂያ ፋብሪካ በ1ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ሊገነባ ነው።ፋብሪካውን የሚገነባው አማ ቢዝነስ ግሩፕ ሲሆን፤ ለሚያስገነባው ፕሮጀክት የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የመሰረተ ድንጋይ ተቀምጧል።በወቅቱ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ፖሊሲ የግል ባለሀብቶችን የሚያበረታታ ነው። በክልሉ ማልማት ለሚፈልጉ መሰል ባለሀብቶችም ለኢንቨስትመንት የሚሆን ምቹ ሁኔታ በመኖሩ ወደክልሉ ሄደው መዋዕለ ንዋያቸውን ሊያፈስሱ ይገባል።የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በበኩላቸው፤ እንደሀገር ለዘይት ምርት በየወሩ 48 ሚሊዮን ብር እንደሚወጣ ገልጸዋል። የሀገራችን የዘይት ፋብሪካዎች 12 በመቶ ብቻ የሚሸፍኑ መሆኑን በመጠቆምም፤ ፕሮጀክቱ እንደ ሀገር የዘርፉን ችግር የሚቀርፍ መሆኑን አስረድተዋል።የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ በበኩላቸው፤ እንደነዚህ ዓይነት ፕሮጀክቶች ሥራ አጥነትን ከመቀነስ አንጻር የጎላ ፋይዳ ያለው ብቻ ሳይሆን የከተማዋንም ተመራጭነት የሚያሰፋ መሆኑን ተናግረዋል። ከተሞችን ለሰው ልጆች ምቹ ለማድረግ አስተዳደሩ ጠንክሮ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።የድርጅቱ ባለቤት አቶ አንድነት ጌታቸው በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ወደ ኢንቨስትመንት መግባታቸውን ገልፀው፤ የዚህ ፕሮጀክት ግንባታ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ ተናግረዋል። ድርጅቱ በፍጥነት እንደሚጠናቀቅ እና ለ2 ሺህ44 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጠርም መናገራቸውን የዘገበው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 19/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38310
[ { "passage": "፡- የኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ካምፓኒ አካል የሆነው የኮካ ኮላ ፋብሪካ በኢትዮጵያ አራተኛና ትልቁን ፋብሪካውን በሰበታ ከተማ ለመክፈት በ2 ቢሊየን ብር\nየግንባታ ሥራውን በይፋ አስጀመረ፡፡ ካምፓኒው ከሰበታ ከተማ በተረከበው 14 ነጥብ ሦስት ሄክታር መሬት ላይ በኢትዮጵያ ትልቁን የኮካ ኮላ ፋብሪካ ለመክፈት የግንባታ ሥራው መጀመሩን ይፋ ባደረገበት ወቅት ግንባታው በሁለት ምዕራፍ እንደሚጠናቀቅ አሳውቋል፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ የፕላስቲክ መጠጦች ፋብሪካ ግንባታ የሚከናወን ሲሆን፤ በሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ የጠርሙስ መጠጦች ፋብሪካ እንደሚገነባ አሳውቋል፡፡ ፋብሪካዎቹ በአጠቃላይ በ2 ቢሊየን ብር እንደሚገነቡና ለአንድ ሺ ሰዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩ ተገልጧል፡፡ በኦሮሚያ ክልል በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር ሃላፊ አቶ አህመድ ቱሳ በመርሃ ግብሩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሰበታ ለአዲስ አበባ ቅርበት ያላትና ለኢንቨስትመንት ምቹ መሆኗን በመጥቀስ የከተማዋ ምልክት የሆነውን አንጋፋውን የሜታ ቢራ ፋብሪካን ጨምሮ ከሰባት መቶ የሚበልጡ ፋብሪካዎች በከተማዋ መገኘታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ይህ የኮካ ኮላ ፋብሪካም ለወጣቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንና አገሪቷ ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለምታደርገው ሽግግር አቅም እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡ የግል ባለ ሀብቶች በአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንዳሉ የተናገሩት አቶ አህመድ፤ የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንፃርም ትልቅ አበርክቶ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ የሰበታ ከተማ\nከንቲባ አቶ ብርሃኑ በቀለ በበኩላቸው እስከ አሁን በከተማው ውስጥ ባሉት የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ከስልሳ ሺ በላይ\nለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረ ገልፀው፤ የዚህ ፋብሪካ መከፈትም ሌላ አቅም እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡ በፋብሪካው ውስጥ የሥራ ዕድል ከሚፈጠርላቸው ዜጎች በተጨማሪ ምርቱ በገበያ ሥርዓት ውስጥ ሲገባ ለዜጎች ሌላ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡ የደቡባዊና ምሥራቃዊ አፍሪካ የኮካ\nኮላ ንግድ ሕብረት ፕሬዝዳንት ቡርኖ ፔትሪሺያ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ፋብሪካው ለአካባቢው ማህበረሰቦች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በተጨማሪ ችግኞችን በመትከል የወዳደቁ ፕላስቲኮችን ዳግም ጥቅም ላይ በማዋል አካባቢን የመጠበቅ ሥራ እንደሚሠራ ተናግረዋል፡፡ የኮካ ኮላ ፋብሪካ\nከአሁን በፊት በአዲስ\nአበባ፣ በድሬደዋ እና በባህርዳር\nከተሞች ተገንብቶ ምርት\nእየሰጠ ሲሆን፤ እስከ\nአሁንም ከ2 ሺ ሁለት\nመቶ የሚበልጡ ቋሚ ሠራተኞ\nአሉት፡፡ አሁን በሰበታ\nበግንባታ ሥራ ላይ የሚገኙ\nከሦስት መቶ በላይ\nሠራተኞች ይገኛሉ፡፡ ካምፓኒው\nበቀጣይም በሀዋሳ ከተማ\nሌላ የማስፋፊያ ፋብሪካ\nለመገንባት በዝግጅት ላይ እንዳለም\nለማወቅ ተችሏል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 14/2011", "passage_id": "4667cc27647f8a3f9ee4ea534e57f384" }, { "passage": "ጎንደር፡- በአማራ ብሔራዊ\nክልላዊ መንግስት ጎንደር ከተማ በቀን ከ10 ሺ ሊትር በላይ ዘይት የሚያመርት ፋብሪካ ዛሬ ተመርቆ ስራ ጀመረ፡፡የፌደራል ህብረት ስራ\nኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር አቶ ኡስማን ሱሩር በምረቃው ወቅት እንደተናገሩት በፀሀይ ሁለገብ የገበሬዎች ኅብረት ስራ ዩኒዬን የተገነባው\nየዘይት ማምረቻ ፋብሪካ በአመት 80ሺህ ኩንታል የቅባት እህል በግብአትነት የሚጠቀም ሲሆን በቀን ከ10 ሺህ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ማምረት ይችላል፡፡ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ\nወጪ የተደረገበት ፋብሪካው ኑግ፣ ለውዝ፣ ሱፍና ሰሊጥን ጨምሮ ሰባት አይነት የቅባት እህሎችን አበጥሮ፣ ፈጭቶና ራሱ በሚያመርታቸው\nከግማሽ ሊትር እስከ ሀያ ሊትር በሚይዙ የፕላስቲክ መያዣዎች አሽጎ ለሀገር ውስጥና ለውጪ ገበያ ያቀርባል፡፡ ፋብሪካው በሀገሪቱ\nየሰሊጥ ዘይት በማምረት የመጀመሪያው ሲሆን ለ52 ቋሚና 24 ግዚያዊ ሰራተኞች የስራ እድል ከፍቷል፡፡የፀሀይ ሁለገብ የገበሬዎች ኅብረት ስራ ዩኒዬን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ እንዳልካቸው አቤ በበኩላቸው ፋብሪካው በሙሉ\nአቅሙ ወደ ማምረት ስራ ሲገባ በዘይት ምርቶች ግብይት ረገድ የሚታየውን ያልተመጣጠነ አቅርቦትና የተጋነነ ዋጋ በማስተካከል መፍትሔ\nእንደሚሆንና አብዛኛውን ግብአት በአካባቢው ካሉአርሶአደሮች የሚጠቀም በመሆኑ በአካባቢው ላሉ የቅባት እህል ምራቾችም የተረጋጋ ገበያ\nለመፍጠር እንደሚጠቅም ተነግሯል፡፡በራስወርቅሙሉጌታ", "passage_id": "f8a87bb25c60b8f9cedcd8e977de817c" }, { "passage": "-በሀገሪቱ ባለፉት 11 ወራት 7 ነጥብ 9 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል ከቤንዚል ጋር በመቀላቀል ገበያ ላይ መዋሉን የውሃ ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ 7 ነጥብ 9 ሚሊየን ሊትር ኢታኖልን ከቤንዚል ጋር ቀላቅሎ ገበያ ላይ በማዋል 6 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር የውጪ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል።የኢታኖል ምርትን በመተሃራና ፊንካ ስኳር ፋብሪካዎች እንደሚመረት የገለፁት አቶ ብዙነህ ምርቱን በመቀላቀል በኩል ደግሞ የናይል፣ ኦይል ሊቢያና የኖክ ማደያዎች ቀላቅለው ለገበያ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል።የኢታኖል ምርት ጥቅም ላይ መዋል ከጀመረበት 2001 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት በአጠቃላይ 38 ነጥብ 54 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል ከቤንዚል ጋር በመቀላቀል ጥቅም ላይ ውሏል ብለዋል።በዚህም ከውጪ ይገባ የነበረውን ቤንዚል ማስቀረት 30 ሚሊየን 200 ሺ ዶላር  የውጭ ምንዛሪን ማዳን መቻሉን ተናግረዋል።በሀገሪቱ እየተካሄደ ካለው ፈጣን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ የነዳጅ ፍላጎት በከፍተኛ ፍጥረት እያደገ መምጣቱን የገለፁት አቶ ብዙነህ በአሁኑ ወቅት በየአመቱ ከ8 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ለነዳጅ ዘይት ግዢ እንደሚውል ገልፀው፤ ይህም የሀገሪቱ የውጪ ምንዛሬ ገቢ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ቀላል የሚባል አይደለም በማለት ተናግረዋል።በመሆኑም በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ መጨረሻ እየተሰሩ ያሉ የስኳር ፋብሪካዎችን ታሳቢ በማድረግ በአመት 181 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል ለማምረት መታቀዱን አቶ ብዙነህ ገልፀዋል።በአገር ውስጥ በሚመረቱ የሀይል ምንጮች ፍላጎቱን በመተካት ለነዳጅ ዘይት የሚወጣውን የወጪ ምንዛሬ ማስቀረት እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለተግባራዊነቱም የተለያዩ እንቅስቃሴዎች በመደረግ ላይ ነው ሲሉ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።", "passage_id": "0c63b3a0fa056b33ea8c09ebf45e7439" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በ10 ቢሊየን ብር እየተገነቡ ያሉ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በዚህ አመት ማምረት እንደሚጀምሩ የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን አስታወቀ።ኮርፖሬሽኑ የቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ፓርክን ጨምሮ ሌሎች የግብዓት አቅራቢ ኢንዱስትሪዎችን ለባለሃብቶች፣ ለማህበራትና ለኢንቨስትመንት ተቋማት የማስተዋወቅ ዓላማ ያለው መድረክ በአዳማ ከተማ አካሄዷል።የኦሮሚያ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሲሳይ ገመቹ በክልሉ ከ10 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የቡልቡላ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክና ሌሎች ስድስት መጋቢ ኢንዱስትሪዎች በግንባታ ላይ ናቸው ብለዋል ።በሻሸመኔ፣ ዶዶላ፣ ባሌ ሮቤ፣ ኢተያ፣ መቂና አርሲ ነገሌ እየተገነቡ ያሉት መጋቢ ኢንዱስትሪዎች ምርትን በቀጥታ ከአርሶ አደሩ በመረከብ ወደ ቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚያስገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።ኢንዱስትሪዎቹ ማምረት ሲጀምሩ ከ100 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ አቶ ሲሳይ ገልጸዋል።በቡልቡላ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ሁለት ኩባንያዎች ገብተው የማሽን ተከላ ስራ እያከናወኑ መሆኑንም ጠቅሰዋል።በተለይም ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮችና ማህበራት ወደ ፓርኩ ገብተው እንዲያለሙ የማበረታታት ስራ እንደሚሰሩም አመላክተዋል።የኦሮሚያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ አበበ ድሪባ ለኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚቀርቡ የግብርና ግብዓቶችን በጥራትና በብዛት ለማምረት ከኮርፖሬሽኑ ጋር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡አርሶ አደሩ ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ በጥራት እንዲያለማ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጡ 103 ማዕከላት መደራጀታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።", "passage_id": "53749ac6730e6dc7d869d1023bbfc17c" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ ) በክልሉ የነዳጅ አቅርቦት ችግርን ለመቅረፍ ተጨማሪ ከ800 በላይ የነዳጅ ማደያዎችን ለመገንባት መታቀዱን የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡በዚህም በአማራ ክልል የነዳጅ አቅርቦት ችግሩን ለመፍታት አዲስ የነዳጅ ማደያ እና የቦታ አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ መውጣቱ ተገልጿል፡፡የአዲስ የወጣውን መመሪያ አስመልክቶ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ እና የከተማ ልማት እና ቤቶች ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊዎች ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ተዋቸው ወርቁ በሰጡት መግለጫ÷ በክልሉ 202 የነዳጅ ማደያዎች መኖራቸውን አስታውቀዋል፡፡እነዚህ የነዳጅ ማደያዎች በአሁኑ ወቅት በአማራ ክልል ለተመዘገቡ 100 ሺህ ተሽከርካሪዎች እንኳን አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ካለማድረጋቸውም ባለፈ ደረጃቸው ዝቅተኛ መሆንም ሌላኛው ችግር ሆኖ መቆየቱን ምክትል ቢሮ ኃላፊው በመግለጫቸው አብራርተዋል፡፡ከዚያም ባለፈ የነዳጅ ዋጋ በመንግስት ተመን የሚመራ መሆን እና ባለሃብቶች በጨረታ እንዲወዳደሩ መደረጉ ፣በቂ የነዳጅ ማከፋፈያ መሰረተ ልማት አለመኖር፣ ለተለያዩ አገልግሎቶች ነዳጅ የሚጠቀመው የኅብረተሰብ ቁጥር እና የነዳጅ አቅርቦት አለመመጣጠንም ሌላኛው ችግር መሆኑንም ነው ያነሱት፡፡ይህም በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ጫና መፍጠሩን አቶ ተዋቸው ወርቁ  አመላክተዋል፡፡ችግሩን ለመፍታትም ጥናት ሲካሄድ መቆየቱንና በጥናቱ መሰረት በክልሉ በተጨማሪ  ከ800 በላይ ማደያዎች እንደሚገነቡ አቶ ተዋቸው አስታውቀዋል፡፡የሚገነቡት የነዳጅ ማደያዎች እስከ ስድስት ታንከሮችን መቅበር የሚያስችሉ እና ሱቆችን፣ ካፍቴሪያዎችን፣ ቢሮዎችን እና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ያካተቱ ይሆናሉ ም ነው የተባለው፡፡የአማራ ክልል የከተማ ልማትና ቤቶች ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወንድምነው ክንዱ  በበኩላቸው÷ ግንባታዎቹ በ2013 ዓ.ም ተጠናቅቀው በ2014 ዓ.ም አገልግሎት እንደሚሰጡ  ተናግረዋል።ማደያዎቹ ተገንብተው ሲጠናቀቁ የክልሉ የነዳጅ ማደያዎች ቁጥር ከ1 ሺህ በላይ ይሆናሉ ማለታቸውን አብመድ ዘግቧል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "121fa10b39aa5602e30f99d220442f16" } ]
8c653737890d60da845dd6358e67fc2d
2f472d0cab46b5a0d3536cdb66ccbed5
የፕሪሚየር ሊጉ የአንደኛ ዙር ቆይታ- ከስፖርታዊ ጨዋነት አንፃር
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመቱ አንደኛ ዙር መርሐ ግብር ከሦስት ወራት ቆይታ በኋላ ባሳለፍነው ሰኞ የካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም ተጠናቋል። የመጀመሪያው ምዕራፍ በተለያዩ ክስተቶች የታጀበ ሆኖም አልፏል።የመጀመሪያው ዙር ቆይታ የኢትዮጵያ እግር ባለፉት ሁለትና ሦስት ዓመታት ከገባበት የስፖርታዊ ጨዋነት ስጋት አንፃራዊ በሆነ መልኩ መሻሻል የታየበት ነው።ፕሪሚየር ሊጉ ሲወቀስበት ከነበረው የስፖርታዊ ጨዋነት ስጋት ወጥቶ አዲስ መልክ እንዲይዝ በማድረግም የሊግ ኮሚቴው ውጤት ማሳየት የጀመረበት ነበር።በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በተለይ ከሦስት ዓመት ወዲህ የስፖርታዊነት ጨዋነት ችግር የእግር ኳሱ ትልቅ ፈተና ሲሆን ታዝበናል። በየጨዋታዎች በደጋፊዎች መካከል የሚነሱ ፀቦች እንደ ፋሽን መታየት የጀመሩበት ጊዜም ነበር። በፌዴሬሽኑ፣ በክለቦች ፣በመንግሥት በኩል ለችግሩ መፍትሔ ማምጣት የሚያስችሉ ሥራዎች እንደተሠሩ ቢነገርም ስታዲየሞችን የፀብ መነኸሪያ ከመሆን መታደግ አልተቻለም ነበር።ስታዲየሞች የእግር ኳስ ስሜትን ሳይሆን የፖለቲካ ስሜትን ማንፀባረቂያ መድረክ ወደ መሆን እስከመሻገር ደርሰዋል።የትግራይና የአማራ ክልል ክለቦች ፤በደቡብ ክልል የሚገኙ ክለቦች እርስ በዕርስ ተገናኝተው ለመጫወት አዳጋች እስከመሆን ያደረሰንም ስርዓት አልበኝነት ሰፍኖ ነበር።በ2009 ዓ.ም በርካታ ቁጥር ያለው የስቴዲየም ሁከት በተለይም በፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ቢከሰቱም ከብጥብጦቹ ጀርባ እግር ኳስን የሚሻገሩ ገፊ ምክንያቶች እምብዛም እንዳልነበሩ ይጠቀሳል። ከ2009 ወዲህ ግን በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚለኮሱ የስቴድየም ግጭቶችና ረብሻዎች ቁጥር ከዘንድሮው የውድድር ዓመት በፊት አይለው ነበር።በ2010 የውድድር ዓመት ሐዋሳ፣ ድሬዳዋ፣ አዲግራት፣ ጅማና ወልዲያ ከተሞች ውስጥ የስቴድየም ሁከትና ግጭቶች ተበራክተው እንደነበር ይታወሳል።በተለይም በውድድር ዓመቱ በወልዲያ ስፖርት ክለብና በመቀሌ ከተማ መካከል ሊደረግ የነበረው የእግር ኳስ ጨዋታ ከመጀመሩ ከሰዓታት በፊት በሁለቱ ቡድኖች ደጋፊዎች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ህይወት የጠፋ ሲሆን ንብረት ላይ ዘረፋና ወድመት ተከስቷል። በዕለቱም ማገባደጃ ላይ በመቀሌ ከተማ መንገዶች ላይ ክስተቱን ለመቃወም በርካታ ሰዎች ወጥተው እንደነበር አይዘነጋም። ጨዋታው ካለመካሄዱ በተጨማሪም የግጭቱ አሻራ እስከ ቀጣይ ቀናት ሲሻገርና ከእግር ኳሳዊ ምክኒያት ይልቅ ፖለቲካዊ አንደምታው ሚዛን ሲደፋ ታይቷል።በወቅቱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ጁነዲን ባሻ ክስተቱ ከእግር ኳስ የሚሻገር ገፅታ እንዳለው ተናግረው ነበር፡፡የ2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ከረብሻዎች ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በተለያዩ ክለቦች ላይ የጣለው ቅጣት ግማሽ ሚሊዮን ብር ገደማ መሰብሰብ መቻሉ ግጭቶች በምን ያህል ደረጃ እንደተበራከቱ ማሳያ ነው።በእንቁላሉ ጊዜ ያልተቀጣው እግር ኳስ ከፖለቲካም በላይ ጦዞ ለፀጥታ አስከባሪዎች ፈተና ከመሆን አልፎ እንደ አገር ስጋት የሆነበት ደረጃ ላይ ደርሶም ነበር።ሰላም በራቃቸው የስፖርት ማዘውተሪያዎች መደበኛ የውድድር መርሐ ግብሮች መተማመኛ ማግኘት አልቻሉም ነበር።በክልል የሚካሄዱ ጨዋታዎች በፖለቲካ ትኩሳት ሳቢያ ተጨማሪ ራስ ምታት እየሆኑ መምጣታቸውም አሳሳቢ ነበር።በስፖርቱ ዓለም የተመልካቾች ነውጠኝነት ምክንያቶች ብዙ መሆናቸውን በስፖርቱ ጥልቅ እውቀት ያላቸው ባለሙያዎች ሲናገሩ ይደመጣል።ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ ወይንም ምጣኔ ሀብታዊ ብሶቶች ስቴዲየም ላይ ሊያጠሉ እንደሚችሉም ይታመናል።በኢትዮጵያ እግር ኳስን የታከከ ግጭትና ሁከት ሲከሰት የመጀመሪያው ባይሆንም በተለይም ባለፈው የውድድር ዓመት ቀይ መስመር አልፎ ነበር።የቅርብ ጊዜ ክስተቶችን ስናጤን ደግሞ ከእግር ኳስ ባሻገር ከእነዚህ ምክኒያቶች ሁሉ ለስፖርት ጠንቅ የሆነ የፖለቲካ አጀንዳ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ራሳቸው አስተውለውታል።እግር ኳስ ማኅበረሰባዊ መሰረት ከሌለው በስተቀር የጠነከረ የእኔነት ስሜት ሊፈጥር አይቻለውም የሚሉ ተንታኞች፤ ክለቦች ከማኅበረሰባዊ መሰረታቸው በዘለለ ብሔር ተኮር መልክን እየተላበሱ የመምጣታቸው አዝማሚያ አደገኛ መሆኑ የበርካታ ስፖርት ቤተሰቦች እምነት ነው፡፡ክለቦች ሲቋቋሙ ወይንም ሲዋቀሩ አካባቢያዊ መገለጫ ወይንም ከተማዊ ስያሜ ሊኖራቸው ቢችልም ከብሔር፣ ከዘር ወይንም ከኃይማኖት ጋር በተቆራኘ መልኩ መደራጀት ክልክል መሆኑን የስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ማኅበራት ማደራጃ መመሪያ አንቀፅ 50 ቁጥር 2 ይገልፃል። ነገር ግን ባለፉት ዓመታት ብቻ ፌዴሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ሊጎች የብሔር ስም የተቀጠላላቸው በርካታ ክለቦች ውድድር እያደረጉ መጥተው ነበር።እግር ኳሱ ከአንዳንድ ሁከቶች አልፎ እጅግ ወደተደራጀ ነውጠኛነት እያመራ ስለመሆኑም ሲነገር ቆይቷል።ቀስ በቀስም ወደ መቧደን እየተጓዘ ነበር።ይህ አዝማሚያ የ2012 ዓ.ም የውድድር ዓመት ከመጀመሩ አስቀድሞ በእግር ኳሱ ላይ ምን ሊፈጠር እንደሚችል በበርካቶች ዘንድ ስጋት ፈጥሮ ነበር።በዚህ ስጋት ውስጥ እያለ ኅዳር 21 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረው ፕሪሚየር ሊግ ከፌዴሬሽኑ መሪነት ወጥቶ በሊግ ኮሚቴ መመራቱን ተከትሎ ቢያንስ ቢያንስ በመጀመሪያው ዙር የታሰበው ስጋት ሊረግብ ችሏል።በውድድር ዓመቱ በመጀመሪያ ዙር ከተደረጉ 30 ጨዋታዎች ቢያንስ 25 ጨዋታዎች ስፖርታዊ ጨዋነት የነገሠባቸው ነበሩ። ስፖርቱን ከፖለቲካ በመቀላቀል ስታዲየሞችን የፀብ መናገሻ የማድረጉ ዝንባሌ እንዳይኖሩ የተደረጉ ጥረቶችም ከሞላ ጎደል ፍሬያማ ነበሩ ማለት ይቻላል።ለዚህ ደግሞ የአማራ ክልልና ትግራይ ክልል ክለቦችን እንደ ማሳያ ማንሳት ይገባል። አምና በሁለቱ ክልል ክለቦች ደጋፊዎች መካከል የነበረውን መፋጠጥ በውድድር ዓመቱ እንዳይደገም ማድረግ ተችሏል። የባህር ዳር ወጣቶች የመቐለ 70 እንደርታ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች በወንድማዊ ስሜት ‹‹እንኳን ወደ ውቢቷ ከተማችሁ በደህና መጣችሁ›› ሲሉ በፍቅር በመቀበል ፀብን ለማራቅ የሄዱበት ርቀት ትልቅ ርምጃ ነበር።የመቐለ 70 እንደርታ ደጋፊዎች ከባህር ዳር ከነማ ደጋፊዎች በጋራ በመሆን ከተማዋን በማፅዳት አንድነታቸውን ያሳዩበት ድርጊት የከረረውን ስጋት መበጠስ ችሏል።የሁለቱ ክለቦች ደጋፊ ማህበራት በአብሮነት መሥራት መቻላቸው ስፖርት ለሰላም፣ ለአንድነትና ለወንድማማችነት መርህን በተግባር እንዲታይ አድርጓል። የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ወደ መቐለ ከተማ ባቀናበት ወቅት የነበረው ሁኔታ ፤በሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች መካከል ተጨማሪ የአንድነት ስሜት እንዲጎለብት ያደረገ ነበር። የመቐለ ከተማ ወጣቶች የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾችና ደጋፊዎችን ፍጹም ፍቅር በተሞላበት መልኩ ተቀብለው በመሸኘት የልዩነቱን ግንብ ማፍረስ የቻሉበትን አጋጣሚ ፈጥረዋል። በሁለቱ ክልሎች የሚገኙ የክለቦች ደጋፊ ማህበራት በኩል የታየው ቆራጥነት ለዚህ ውጤት መገኘት ትልቅ ድርሻ የያዘም ነበር። የሁለቱ ክልሎች የመንግሥት አመራሮች በኩል የታየው ቀናኢነትና ከደጋፊ ማህበራቱ መቀናጀት ጋር ተደምሮ የእግር ኳሱ ስጋት ሊረግብ ችሏል። በደቡብ ክልል የሚገኙ ክለቦች ደጋፊዎች ስፖርታዊ ጨዋነት እንዲሰፍን ያሳዩት ቁርጠኝነትም የመጀመሪያው ዙር አንፃራዊ ሰላም እንዲሰፍንበት ትልቅ ሚና ነበረው።በወላይታ ድቻና ሲዳማ ቡና ክለብ ደጋፊዎች መካከል የነበረውን መፋጠጠ በውድድር ዓመቱ አዲስ የሰላም መልክ መያዝ መቻሉ ለዚህ ስኬት ምሳሌ ነው፡፡ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውበት ከሆኑ ክለቦች መካከል የሸገር ደርቢዎቹ ኢትዮጵያ ቡናንና ቅዱስ ጊዮርጊስን እዚህ ላይ ሳይጠቅሱ ማለፍ አይቻልም።የከተማዋ ተፎካካሪ ክለቦች ቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ተመልካቾች መካከል የተስተዋለው መከባበርና ሥነ ሥርዓት ለክልል ክለብ ደጋፊዎች እንደማሳያ መወሰድ እንዳለበት የብዙኃን አስተያየት ጭምር ነበር።ቀደም ሲል ሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ሲኖራቸው በከተማዋ የሚኖረው ውጥረትና የፀጥታ ስጋት በዚህ ዓመት ከከተማዋ ዋንጫ ጀምሮ ሰላማዊና የሚያስመሰግናቸው ጭምር ነበር።የሁሉም ክለቦች ደጋፊ ማኅበር ፕሬዚዳንቶች በጥምረት የመሠረቱትን ማኅበር ተከትሎ፣ እንደዚህ ዓይነት ችግሮች ዳግም እንዳይከሰቱ የሸገር ደርቢዎች የነበራቸውን ሚናም በጉልህ የሚጠቀስ ነው።የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ሚና ከዚህ ስኬት ጋር አብሮ መነሳት ይገባዋል። ከንቲባው በተለያዩ ጊዜያት ከኢትዮጵያ ቡና እና የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፖርት ክለብ አመራሮች ጋር በወቅታዊ እና መሠረታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በመወያየት በደጋፊዎች መካከል ይፈጠር የነበረውን ግጭት እንዲከስም ያላሳለሰ ጥረት ሲያደርጉ ነበር። በሸገር ደርቢ ጨዋታ ወቅት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይሰማ የነበረው የፀብ ዜና በሰላም እንዲተካ በማድረግ ረገድ ምክትል ከንቲባውና የሁለቱ ክለቦች ደጋፊ ማህበራት ቆራጥነት ሳይደነቅ የሚታለፍ አይደለም።የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2012 ዓ.ም የውድድር ዓመት አንደኛ ዙር ቆይታ ከስፖርታዊ ጨዋነት አኳያ አበረታች ውጤት የታየበት ቢሆንም በመጨረሻዎቹ ሁለትና ሦስት ጨዋታዎች እንከኖች መታየታቸው አልቀረም።ኢትዮጵያ ቡና ከወላይታ ድቻ በነበራቸው ጨዋታ፣ ወልቂጤ ከተማና ሲዳማ ቡና በነበራቸው ጨዋታ በደጋፊዎች መካከል የተፈጠረ ግጭት ቢኖርም እንዳለፉት ዓመታት የተጋነነ ነው ለማለት አይቻልም።ያም ሆኖ የሊግ ኮሚቴው እንዲህ ዓይነት ግጭቶች ወደ ሁለተኛው ዙር እንዳይዛመቱ ሰሞኑን ፋሲል ከነማንና ቅዱስ ጊዮርጊስን ከዚሁ ከስፖርታዊ ጨዋነት ጋር በተያያዘ ቅጣት እንዳስተላለፈባቸው ሌሎቹንም ተመልክቶ ፍትሐዊ ቅጣት ማስተላለፍ ይጠበቅበታል።ይህም ሳይቃጠል በቅጠል እንዲሉ የመጀመሪያው ዙር በተሻለ ስፖርታዊ ጨዋነት እንደተጠናቀቀው ሁሉ ለሁለተኛውም ዙር ከወዲሁ የቤት ሥራዎችን ጨርሶ መሻገር ለነገ የሚባል አይደለም።አዲስ ዘመን አርብ የካቲት 20/2012ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28042
[ { "passage": "በ2፡00 በተደረገው ጨዋታ ሆሳእና ከነማ ጅማ ከነማን 3-1 አሸንፏል፡፡ትላንት በተላለፈ ውሳኔ 4 ጨዋ እና 3 ሺህ ብር ተቀጥተው የነበሩት የጅማ ከነማው አሰልጣኝ ፋንታዬ አባተ የጨዋታ ቅጣቱ ተነስቶላቸው ቡድናቸውን ቢመሩም ከመሸነፍ አልዳኑም፡፡ግብ በማስቆጠር ቅድሚያውን የያዙት ጅማዎች ሲሆኑ አሸናፊ ይታየው በ17ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ መምራት ችለው ነበር፡፡ በ24ኛው ደቂቃ ሀብቶም ገ/እግዚአብሄር ግብ አስቆጥሮ ሆሳእና ከነማን አቻ አድርጓል፡፡ ከእረፍት መልስ በ62ኛው ደቂቃ የጨዋታው ኮከብ ዱላ ሙላቱ ሆሳእናን መሪ ሲያደርግ ጨዋታው ሊገባደድ ሽርፍራፊ ሴኮንዶች ሲቀሩ አምረላ ደልታ የሆሳእናን ድል አስተማማኝ አድርጎታል፡፡ከጨዋታው በኋላ የሆሳእና ከነማው አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ በሰጡት አስተያየት ወደ ፕሪሚር ሊጉ ከመግባት የሚያግዳቸው ነገር እደሌለ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ ጅማ ከነማን እንደምናሸንፍ አስቀድመን ተናግረን ነበር፡፡ ነገር ግን በሜዳ ላይ ፈትነውን ነበር፡፡ እኛም ያገኘናቸውን እድለች በአግባቡ አልተጠቀምንም፡፡ በማሸነፋችን ደስተኞች ነን፡፡››‹‹ በግማሽ ፍፃሜው የምንገጥመውን ቡድን በሚገባ እናውቀዋልን፡፡ (ሀላባ ከነማ) ከዞናችን የመጣ ቡድን በመሆኑ አጨዋወታቸውን እናውቀዋለን፡፡ ወደ ፊት ከመጓዝ የሚያግደን ነገር የለም›› ብለዋል፡፡የተሸናፊው ቡድን አሰልጣኝ ፋንታዬ አባተ በበኩላቸው በስነልቡናው ረገድ አለመዘጋጀታቸው ውጤት እናዳሳጣቸው ተናግረዋል፡፡ ‹‹ ከሼር ኢትዮጵያ ጋር በተፈጠረው ውዝግብ ምክንያት ተረብሸናል፡፡ ያንን እያሰብን ወደ ሜዳ ስለገባን በስነልቡናው ረገድ የማሸነፍ ዝግጁነት አልነበረንም፡፡ በጨዋታው የበለጠው ቡድን አሸንፏል፡፡ ሆሳእናዎች እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ የድሬዳዋ ህዝብንም ማመስገን እፈልጋለሁ፡፡ ›› ብለዋል፡፡ሆሳእና ከነማ በግማሽ ፍፃሜው ሃላባ ከነማን የሚገጥም ሲሆን ካሸነፈ በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ፕሪሚየር ሊግ መግባቱን ያረጋግጣል፡፡ ሁለቱ ቡድኖች እርስ በእርስ የሚጫወቱ በመሆናቸው አንድ የደቡብ ክለብ ፕሪሚየር ሊግ ከመግባቱ በተጨማሪ ከሁለቱ አንዳቸው በፕሪሚየር ሊጉ የተሳተፉ 43ኛው ክለብ ይሆናሉ፡፡ ፎቶ – ከላይ የሆሳእና ተጫዋቾች ከድሉ በኋላ ፣ መካከል – የሆሳእናው አሰልጣኝ ግርማ ፤ ከታች የጨዋው ኮከብ ተብሎ በድሬዳዋ ስፖርት ኮሚሽን እና ወጣቶች ቢሮ በጋራ የተመረጠው ዱላ ሙላቴ", "passage_id": "1d87ae94990ab650f05f4d07c6d5bf12" }, { "passage": "በኢትዮጵያ ብሄራዊ ሊግ ወሳኝ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ሆሳእና ከነማ ሃላባ ከነማን 3-0 አሸንፎ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ መግባቱን አረጋግጧል፡፡የሀላባ ከነማ ደጋፊዎች የቡድናቸውን ወሳኝ ጨዋታ ለመከታተል ወደ ድሬዳዋ በሚያመሩበት ወቅት አሰበ ተፈሪ ላይ በደረሰ አደጋ 4 ደጋፊዎች ህወታቸው ማለፉን ተከትሎ ጨዋታው በ1 ደቂቃ የህሊና ፀሎት ተጀምሯል፡፡ሆሳእና ከነማ በወሳኝ ተጫዋቾቹ ግቦች ታግዞ 3-0 ባሸነፈበት ጨዋታ ዱላ ሙላቱ በ45ኛው ቴዎድሮስ መንገሻ በ64ኛው እንዲሁም ተዘራ አቡቴ በ82ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡ የዛሬዎቹ ግቦች በአጠቃላዩ ውድድር ለተዘራ 4ኛ ፣ ለቴዎድሮስ 3ኛ እንዲሁ ለዱላ 2ኛ ግባቸው ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ከጨዋታው ፍፃሜ በኋላ ለሶከር ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡት የሆሳእና ከነማው አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ሃላባ ከነማን ማወቃቸው ጨዋታውን ለማሸነፋቸው ምክንያት እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ ‹‹ ሃላባ ከነማ በዞናችን የሚገኝ ቡድን በመሆኑ ስለ አጨዋወታቸው እናውቃለን፡፡ ከጨዋታው በፊትም አሸንፈናቸው ወደ ፕሪሚየር ሊጉ እንደምናልፍ እርግጠኞች ነበርን፡፡ ጨዋታውን በሚገባ ተቆጣጥረን አሸንፈን ወጥተናል›› ብለዋል፡፡የጨዋታውን ሁለተኛ ግብ ያስቆጠረው ቴዎድሮስ መንገሻ የጨዋታው ኮከብ ተብሎ በስፖርት ኮሚሽን እና ወጣቶች ቢሮ በጋራ ተመርጧል፡፡በመጪው እሁድ ከሌላኛው የግማሽ ፍፃሜ አሸናፊ ጋር የፍፃሜ ጨዋታውን የሚያደርገው ሆሳዕና ከነማ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ሲያልፍ በታሪኩ ለመጀመርያ ከመሆኑ በተጨማሪ ከሃድያ ዞን ወደ ፕሪሚየር ሊግ የገባ የመጀመርያው ክለብ ለመሆን በቅቷል፡፡ በፕሪሚየር ሊጉ በመሳተፍ ደግሞ 43ኛው ክለብ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡", "passage_id": "befb853329907f869895108477e85eac" }, { "passage": "መከላከያ በቅርብ አመታት ለዚህ ውድድር የተሰራ እስኪመስል ድረስ ድንቅ አቋም እያሳየ ይገኛል፡፡ ዘንድሮው በ4 አመት ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ ወደ ፍጻሜው ያለፈ ሲሆን በሁለቱ ፍጻሜዎች ሀዋሳ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፎ ዋንጫ አንስቷል፡፡በዘንድሮው የውድድር ዘመን ከሌሎች ተጋጣሚዎች በተለየ መልኩ ጥሩ አቋም ከማሳየታቸው በተጨማሪ ወደ ፍፃሜ ያለፉት ንግድ ባንክን በቀላሉ አሸንፈው ነው፡፡ የክለቡ አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ግን የጥሎ ማለፍ ስፔሸሊስት መሆናቸውን ለማሳየት የነገውን ጨዋታ ማሸነፍ እንደሚገባቸው ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡ ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡አሰልጣኝ ገብረመድህን ስለነገው ጨዋታ ተጋጣሚያቸው ቅዱስ ጊዮርጊስ በሰጡት አስተያየትም ፈረሰኞቹ በቅርቡ የሊጉ ቻምፒዮን በመሆናቸው በጠንካራ ራስ መተማመን ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡ ‹‹ጨዋታው የፍጸሜ እንደመሆኑ መሸናነፍ ግዴታ ነው፡፡ በተደጋጋሚ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ስንገናኝ እነሱም ያሸንፉናል ፣ እኛም እናሸንፋቸዋለን፡፡ ስለዚህ ነገ እነሱ ለማሸነፍ እንደሚጫወቱት እኛም ድል አድርገን ዋንጫ ለማንሳት ነው የምንጫወተው፡፡ ››የመከላከያ የማጥቃት መሳርያ የሆነው ፍሬው ሰለሞን በክለቡ ስኬት ደስተኛ መሆኑን በመግለጽ ጨዋታውን ለማሸነፍ እንደተዘጋጁ ተናግሯል፡፡  ብሏል፡፡ከሳምንት በፊት የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ያነሳው ቅዱስ ጊዮርጊስ በጥሎ ማለፉ ሁለት ጨዋታዎች ከአርባምንጭ እና አዳማ ከተማ ፈተና ቢገጥመውም ፍጻሜውን ከመቀላቀል ያገደው ነገር የለም፡፡ በነገው እለትም ከ2001 በኋላ የሁለትዮሽ ድል ለማስመዝገብ በማለም ወደ ሜዳ ይገባል፡፡ የክለቡ ረዳት አስልጣኝ ፋሲል ተካልኝም ቅዱስ ጊዮርጊስ ምንጊዜም ክብርን እንደሚያስቀድም ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡ ብለዋል፡፡በሩብ ፍጻሜው አርባምንጭ ከተማን ሁለት ጊዜ ከመመራት አንሰራርተው እንዲያሸንፉ የረዳውና አዳማ ከተማን በመለያ ምት ሲረቱ የማሸነፍያ ገሉን ያስቆጠረው አዳነ ግርማም የፋሲል ተካልኝን ሀሳብ የሚያጠናክር አስተያየት ሰጥቷል፡፡ ብሏል፡፡አዳነ ግርማ ከጨዋታው ጎን ለጎን የጸጥታ ስጋት እና የደጋፊዎች ስርአት አልበኝነት አሳሳቢ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ብሏል፡፡መከላከያ በመጀመርያው ዙር ወላይታ ድቻን በቀላሉ 3-0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍፃሜ ሲሸጋገር በሩብ ፍፃሜው ደደቢትን በባዬ ገዛኸኝ የመጨረሻ ደቂቃ ግብ 1-0 አሸንፎ ግማሽ ግፃሜውን ተቀላቅሏል፡፡ ትላንት ደግሞ ንግድ ባንክን በግማሽ ፍፃሜው ገጥሞ 3-0 በማሸነፍ ለፍፃሜው መብቃት ችሏል፡፡ተጫወተ – 3አስቆጠረ – 7ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ – ባዬ ገዛኸኝ (3)ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለፈው የውድድር ዘመን ፕሪሚየር ሊግን በቻምፒዮንነት በማጠናቀቁ በቀጥታ ወደ ሩብ ፍፃሜ ሲያልፍ ቅዳሜ እለት አርባምንጭ ከተማን ሁለት ጊዜ ከኋላ ተነስቶ በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍፃሜ ተሸጋግሯል፡፡ ትላንት ከአዳማ ከተማ ጋር በመደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 1-1 ተለያይቶ በተሰጠው የመለያ ምት ወደ ፍፀሜ አልፏል፡፡ተጫወተ – 2አስቆጠረ – 4ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ – ሳላዲን ሰኢድ እና አዳነ ግርማ (2)በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ እንደ ሁለቱ ክለቦች በዋንጫዎች ያሸበረቁ ክለቦች የሉም፡፡ የቀድሞው ኃያል ክለብ መከላከያ ከረጅም ጊዜያት መጥፋት በኋላ በቅርብ አመታት ዋንጫዎችን ማንሳት የጀመረ ሲሆን ጥሎ ማለፉን ለ13 ጊዜ በማንሳት ባለ ሪኮርድ ክለብ ነው፡፡ፕሪሚየር ሊጉን ከሳምንት በፊት ያነሳው ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደ ፕሪሚየር ሊጉ በጥሎ ማለፉ የቅርብ አመታት ታሪክ በርካታ ዋንጫዎችን ባያነሳም ከአዲሱ ሚሌንየም ወዲህ በተደረጉ ውድድሮች ዋንጫዎችን ለማንሳት ተቃርቦ ነበር፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአጠቃላይ 10 ዋንጫዎችን በማንሳት ከመከላከያ ቀጥሎ በጥሎ ማለፉ ስኬታማ ክለብ ነው፡፡ሁለቱ ክለቦች 2008 ከገባ ወዲህ 6 ጊዜያት ተገናኝተዋል፡፡ ከ2007 ወደ 2008 በተሸጋገረው የጥሎ ማለፍ ግማሽ ፍፃሜ መከላከያ 2-1 ሲያሸንፍ በአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ቅዱስ ጊዮርጊስ በመለያ ምቶች አሸናፊ ሆኗል፡፡ በአአ ከተማ አምበር ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ 4-1 ሲረታ በዚሁ ውድድር ለደረጃ ባደረጉት ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ 2-1 አሸንፏል፡፡ በፕሪሚየር ሊጉ የመጀመርያ ዙር ቅዱስ ጊዮርጊስ 2-0 ሲያሸንፍ በሁለተኛው ዙር 1-1 አቻ ተለያይተዋል፡፡በቅዱስ ጊዮርጊስ ሮበርት ኦዶንካራ በጉዳት የማይሰለፍ ሲሆን ምንያህል ተሾመ የሚገኘው ካናዳ በመሆኑ ከነገው ጨዋታ ውጪ ሆኗል፡፡ተስፋዬ አለባቸው ከ5 ጨዋታ ቅጣት ሲመለስ ራምኬል ሎክ ከመጠነኛ ጉዳቱ  አገግሞ ለነገ ጨዋታ ዝግጁ ሆኗል፡፡በመከላከያ በኩል አስቀድመው የረጅም ጊዜ ጉዳት ያለባቸው ሙሉአለም ጥላሁን ፣ ነጂብ ሳኒ እና ምንይሉ ወንድሙ የማይኖሩ ሲሆን የጥሎ ማለፉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ባዬ ገዛኸኝ በጉዳት ከጨዋታው ውጪ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡", "passage_id": "3600fa315e9a7d05e86cd5683647337e" }, { "passage": " የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ስያሜውን ይዞ መካሄድ ከጀመረ ከሁለት አሥርታት በላይ አስቆጥሯል። ፕሪሚየር ሊጉ እነዚህን ዓመታት ባደረጋቸው ረጅም ጉዞዎች ስያሜውንና ዕድሜውን የሚመጥን ዕድገት እንደሌለው በርካቶች ያነሳሉ። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስያሜ ለውጡን ‹ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ዕድገት በሚል ብቻ ጥናት ሳይደረግ ውድድር መጀመሩ ለዕድገቱ መቀጨጭ የራሱን ድርሻ አበርክቷል ›ሲሉ የሚተቹ በርካቶች ናቸው። ለዚህ በትልቁ የሚጠቀሰው ፕሪሚየር ሊጉን ጨምሮ 98 በመቶ የአገሪቱ ክለቦች በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ከመንግሥት ቋት በመሆኑ እግር ኳሱ ገበያ ተኮር እንዳይሆን አድርጎታል። ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ማንሰራራት የጀርባ አጥንት የሆነውን ፕሪሚየር ሊግ ጠንካራ ማንነት ማላበስ የሚያስችለን አሰራርና አደረጃጀት ማበጀት ያስፈልጋል የሚሉ ድምጾች ሲሰሙ ኖረዋል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የእግር ኳስ ችግር መፍቻ መፍትሄ አንዱ የሊግ አደረጃጀትን ማሻሻል መሆኑን በማመን በ2011 ዓ.ም አጋማሽ ላይ አደረጃጀቱን ለመቀየር ለውይይት ክፍት ባደረገ መልኩ እንቅስቃሴውን አጠናክሯል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዓምና በተቋቋመው «የሊግ ካምፓኒ» እየተመራ ነበር አዱሱን የለውጡን ጅማሮ «ሀ» ያለው። በብሔራዊ ፌዴሬሽንና ክለቦች የጋራ ጥረት ራሱን ችሎ ፕሪሚየር ሊጉን እየመራ ያለው የሊግ ካምፓኒው ከሰሞኑ ያስተላለፈው ውሳኔ በእጅጉ እያነጋገረ ይገኛል። የሊግ ካምፓኒው በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ሐሙስ ሐምሌ 16 ቀን 2012 ዓ.ም. ውይይት አድርጎ ነበር። የኢትዮያ ፕሪሚየር ሊግ ሊግ ካምፓኒ አመራሮቹ ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል «የሊጉን የጥራት ደረጃ ከመጠበቅ ጀምሮ ክለቦቹን ለተለያዩ ችግሮችና አለመግባባቶች ሲዳርጉ ቆይተዋል» በሚል ማሻሻያና ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸው የውድድር ደንብና መመሪያዎች ላይ ውይይት ተደርጓል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሊግ ኩባንያው አዲስ የውድድር ደንብና መመሪያን አጽድቋል። የፕሪሚየር ሊጉ አዲሱ የውድድር መመሪያ በ2021 የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ እና የኮንፌደሬሽን ካፕ ላይ ኢትዮጵያ ተወካይ አልባ አድርጓታል መባሉን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል።የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር መመሪያ በሀገራችን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቢታወጅ እና ያልታሰበ ድንገተኛ ችግር ተፈጥሮ ውድድር ቢቋረጥ በምን መልኩ ውጤት ይሰጥ የሚል የተቀመጠ መመሪያ (ደንብ) አልተዘጋጀም። ስለዚህ አሸናፊ፣ ወራጅ እና በአፍሪካ መድረክ ሀገሪቱን የሚወክል ክለብ በምን መልኩ ይሳተፍ የሚል ህግ እንዳልተቀመጠ ዘገባው አትቷል። የሊግ ካምፓኒ አመራሮች ባደረጉት ውይይት በቀጣይ የውድድር ዘመን በሀገራችን አሁን የተፈጠረው የኮሮና ቫይረስ አልያም ሌላ ከአቅም በላይ ችግር ቢከሰት በምን መልኩ እደሚስተናገድ የሚያስችል አዲስ መመሪያ አውጥተዋል ያለው ዘገባው፤ በመጀመሪያ ደረጃ ውድድሩ ከ75 % ያህል ጨዋታው ተከናውኖ ከሆነ እና ውድድሩ ቢቋረጥ ባለው ውጤት መሠረት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የያዘው ክለብ በካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ እንዲሳተፍ ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው ክለብ ደግሞ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እንዲካፈል ይደረጋል። በወራጅ ላይ የሚገኙ ሶስት ክለቦች በውጤታቸው መሠረት እንዲወርዱ እና በምትካቸው ከከፍተኛ ሊግ አዳጊ ክለቦች እንዲኖሩ በአዲሱ መመሪያ መካተቱን አትቷል።የሊግ ካምፓኒው ውድድሩ ምናልባት ከ65 እስከ 70% ደረጃ ላይ ደርሶ በተለያዩ ምክንያቶች\nቢቋረጥና ውድድሩ በዛው ዓመት ለመቀጠል\nአስቸጋሪ ሁኔታዎች ከሌሉ ምን መደረግ አለበት ለሚለው ውሳኔ አስተላልፏል።\nበውድድር ዓመቱ በፕሪሚየር\nሊጉ አንደኛና ሁለተኛ ሆነው ያጠናቀቁ\nቡድኖች ኢትዮጵያን በአፍሪካ\nመድረክ መወከል እንደሚችሉ\nወስኗል። በዚህ መሰረት የሊግ ኩባንያው\nሊጉን ለመምራት አዲስ ባፀደቀው መመሪያ መሰረት በኢትዮጵያ\nፕሪሚየር ሊግ የ2012\nውድድር ዘመን አሸናፊ ወራጅ እና አዳጊ ክለብ የማይኖር መሆኑን መወሰኑን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል።በ2012 የውድድር ዘመን 56% ላይ የተቋረጠ በመሆኑ፤ አስቀድሞ አጋዥ የሆነ በመመሪያ የተደገፈ ደንብ ባለመኖሩ የሊግ ኩባንያው አስቀድሞ ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዓመት የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ እና የኮንፌደሬሽን ካፕ ላይ እንደማትሳተፍ ባስተላለፈው ውሳኔ እንዲፀና ተደርጓል ብሏል። የሊግ ኮሚቴው ውሳኔ ተከትሎ የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብና መቐለ ሰብዓ እንደርታ በአህጉራዊ መድረክ ላይ ሊሳተፍ ይችሉ ይሆና የሚሉ የተስፋ አስተያየቶች ፉርሽ ያደረገ ተብሏል።የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2012 ውድድር ዓመት\nበኮቪድ 19 ምክንያት\nመቋረጡን ተከትሎ፣ በ‹‹አሸናፊ፣ ወራጅና ወጪ በ2013\nውድድር ዓመት በአፍሪካ\nመድረክ የሚሳተፍ ቡድን የለም፤›› በማለት ሊግ ካምፓኒው\nያሳለፈውን ውሳኔ፣ በተለይ የፕሪሚየር ሊጉ ውድድር እስከሚቋረጥ\nአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የነበሩት\nፋሲል ከተማና መቐለ ሰብዓ እንደርታ\nበአኅጉራዊ መድረክ የመሳተፍ\nዕድል ሊኖረን ይገባል በሚል ውሳኔውን\nመቃወማቸው አይዘነጋም። የፋሲል ከተማ እግር ኳስ ክለብ ለሊግ ካምፓኒው\nውሳኔው ትክክለኛና ተገቢ እንዳልሆነ ጉዳዩን በደብዳቤ ሲገልጽ ቢቆይም፣ ምንም ዓይነት ምላሽ ሳያገኝ ቆይቶም ነበር።አዲስ ዘመን ሐምሌ 21/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "fcc23edbdff1e39146c76ebdf911645a" }, { "passage": "(በአብርሀም ገ/ማርያም እና ዮናታን ሙሉጌታ)ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ጅማ አባ ጅፋር የሻምፒዮንነት አክሊሉን ለመድፋት ዛሬ 8፡00 ላይ የ30ኛ ሳምንት ጨዋታዎቻቸውን ያደርጋሉ። እኛም በዛሬው ፅሁፋችን በታሪክ እስከመጨረሻው የዘለቁ ፉክክሮች እና የሁለቱ ቡድኖች የውድድር አመት ጉዞ ላይ አተኩረናል።\nየ2010 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር አመት ሲነሳ በስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል የተከሰቱ መጥፎ ትዝታዎችን ለማስታወስ መገደዳችን የሚቀር አይሆንም። ነገር ግን አምስት ክለቦችን እስከ መጨረሻዎቹ ጥቂት ሳምንታት ያፎካከረው እና አሸናፊውን ለመለየት እስከ 30ኛው ሳምንት ድረስ እንድንጠብቅ ያደረገን የውድድር አመት መሆኑ አመቱን በክፉ ብቻ እንዳናስታውሰው ያደርገናል። ላለፉት ሰባት የውድድር አመታት መሰል ፉክክሮችን መመልከት አለመቻላችን ደግሞ የዘንድሮው የዋንጫ ፍጥጫ ይበልጥ ትኩረታችንን እንዲስብ የሚያስገድድ ነው። ብርቅ ሆኖ የታየን ይህ ፉክክር ግን በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ታሪክ የመጀመሪያው አይደለም። በርግጥ በአብዛኞቹ አመታት ሻምፒዮኑን ለመገመት የሚያዳግት ፍልሚያ ባንመለከትም ሊጋችን ጨርሶ ፉክክር አልባ ሆኖ የዘለቀም አይደለም። እዚህ ላይ ታሪክ አንገት ለአንገት ተናንቀው አመቱን ስለጨረሱ ቡድኖች ምን እንደሚያሳየን መመልከቱ ተገቢ ይሆናል።በ1990 ፕሪምየር ሊጉ በአዲስ መልክ በ8 ክለቦች ሲጀመር ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጵያ መድን በእኩል 32 ነጥቦች አጠናቀዋል። ከመድን በ2 ጎል የተሻለ ልዩነት ያስመዘገበው የያኔው መብራት ኃይል የአሁኑ ኢትዮ ኤሌክትሪክም ቻምፒዮን መሆን ችሏል። ከዛ ወዲህ በ1991 እና 1992 እና 1994 ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ኤሌክትሪክ በ1993 ሳይቸገሩ ዋንጫውን ሲያነሱ በ1995 እና 1996 የሊጉ የልብ ምት ከፍ ያለበት ወቅት ነበር። በ1995 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የመጨረሻው ጨዋታ ለቻምፒዮንነት የ90ኛ ደቂቃ የኤሪክ ሙራንዳ የማሸነፍያ ጎል አስፈልጎት ነበር። በ1996 ደግሞ ልክ እንደዘንድሮው ዋንጫው ሁለት ቦታ ተቀምጦ በተደረጉ ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ ኒያላን 3-1 አሸንፎ ከኢትዮጵያ ቡና በላይ በማጠናቀቅ ለመጀመርያ ጊዜ የክብሩ ባለቤት ሆኗል። ከሁለት ተከታታይ ልብ አንጠልጣይ የመጨረሻ ሳምንት ትዕይንቶች በኋላ ለተከታታይ ዓመታት ሊጉ የአንድ ክለብ የበላይነት ጎልቶ ታይቶበታል። በ1997 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተከታዩ በ18 ነጥቦች ርቆ ቻምፒዮን ሲሆን በ1998 ፈረሰኞቹ ከቡና በ4 ነጥብ ርቀው ደግመውታል። 1999 ላይ በ21ኛው ሳምንት 11 ክለቦች ያቋረጡትን ውድድር ሀዋሳ ከተማ ሲያሸንፍ በ2000፣ 2001 እና 2002 ቅዱስ ጊዮርጊስ በቀላሉ አሸናፊ ሆኗል። በ2003 የሊጉ ትኩሳት ከዓመታት በኋላ ሲጨምር ሶስት ክለቦች የቻምፒዮንነት ዕድል ይዘው በተደረገው መጨረሻ ሳምንት ኢትዮጵያ ቡና የአሸናፊነት ዘውዱን ደፍቷል። ይህም ከ7 ዓመት በኋላ አሸናፊው በመጨረሻ ቀን የታወቀበት የመጀመርያው ውድድር መሆኑ ነው። ነገር ግን ሊጉ ከ2003 ወዲህ የአጓጊነት መንፈሱን አጥቶ ቆይቷል። በ2004 ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ በ2005 ደደቢት፣ ከ2006-2008 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመጨረሻው ሳምንት ቀደም ብለው ዋንጫውን ማሸነፋቸውን አረጋግጠዋል።ከታሪክ ጋር በተያያዘ የሚነሳ ሌላም ግጥምጥሞሽ አለ። ይኽውም በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ20 ዓመታት ጉዞ ዘንድሮ ጅማ አባጅፋር ለማሳካት የተቃረበውን ታሪክ እስካሁን አሳክቶ የሚያውቀው አንድ ክለብ ብቻ መሆኑ ነው። ቅዱስ ጊዮርጊስ። በ1990 በፕሪምየር ሊጉ ያልተሳተፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ በወቅቱ ሁለተኛ የሊግ እርከን በነበረው በክልል ክለቦች ሻምፒዮና ቀዳሚ ሆኖ በማጠናቀቅ ሙገር እና ምድር ባቡርን አስከትሎ ወደ ፕሪምየር ሊግ አደገ። በ10 ክለቦች መካከል በተደረገው ውድድርም በ18 ጨዋታዎች ከተከታዩ ሀዋሳ ከተማ በ8 ነጥቦች ርቆ በ47 ነጥቦች ቻምፒዮን በመሆን ወደ ሊጉ ባደገበት ዓመት ዋንጫ የማንሳት ብቸኛ ታሪክን ፅፏል። ከ19 ዓመታት በኋላ በመጀመርያ የሊግ ተሳትፎው አስደናቂ ጉዞ ያደረገው ጅማ አባ ጅፋርም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር አንገት ለአንገት ተናንቆ ዛሬ አዳማ ከተማን ይገጥማል። ይህን አስደናቂውን ጉዞውን በዋንጫ ካገባደደው ደግሞ የቅዱስ ጊዮርጊስን የ1991 ታሪክ የሚደግም ይሆናል።የዛሬውን የ30ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ስናስብ ሌላው የሚያስገርመን ነገር ቡድኖቹ እዚህ ከመድረሳቸው በፊት ያሳለፉት የውድድር አመት ነው። እንደሁል ጊዜው ለዋንጫው ግምት ተሰጥቶት ወደ ውድድሩ የገባው ቅዱስ ጊዮርጊስም ሆነ ከከፍተኛ ሊጉ አድጎ ያልታሰበ አመት ያሳለፈው ጅማ አባ ጅፋር በደረጃ ሰንጠረዡ አናት መገኘት የቻሉት አመሻሹ ላይ ነበር። በውድድሩ መሀል በጣም የተዳከሙባቸው እና የውጤት ማሽቆልቆል ያሳዩባቸው ጊዜያት እንደነበሩም የምናስታውሰው ነው። ምንም እንኳን በቶሎ ሽንፈትን ባያስተናግድም የወትሮው ጥንካሬውን ሳያሳይ ጉራማይሌ ውጤት እያስመዘገበ እስከ 11ኛው ሳምንት የዘለቀው ቅዱስ ጊዮርጊስ ሶዶ ላይ በወላይታ ድቻ የአመቱን የመጀመሪያ ሽንፈት ካስተናገደ በኋላ ዳግም ወደ ውጤታማነት ለመመለስ ሌሎች አምስት ሳምንታትን ጠብቋል። በነዚህ ጊዜያት ሶስት ግቦችን ብቻ አስቆጥሮ ብዙዎቹን ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ሲያገባድድ በሀዋሳ ከተማ የደረሰበት የ4-1 ሽንፈትም የማይዘነጋ ነበር። ነገር ግን ፈረሰኞቹ መንገዳቸውን በማስተካከል ከዚህ በኃላ 22ኛው ሳምንት ላይ በአርባምንጭ ከተማ 3-0 ከመሸነፋቸው ውጪ 8 ጨዋታዎችን በድል በመደምደም እና በአራቱ ነጥብ በመጋራት ወደላይ ተስፈንጥረዋል። በ28ኛው ሳምንት ወላይታ ድቻን 4-0 ከረቱ በኋላ ደግሞ ሊጉን መምራት ጀምረዋል። የጅማ አባ ጅፋር የሊግ ጉዞም ዝቅታዎችን ያስተናገደባቸው ጊዜያት ነበሩ። ከታች ያደገ ክለብ እንደመሆኑ ማንም ከዋንጫ ፉክክሩ ጋር ስሙን ያላነሳው አባ ጅፋር አመቱን በድል ቢጀምርም በመቀጠል የደረሱበት ሶስት ተከታታይ የ1-0 ሽንፈቶች ግን ከጅምሩ ከመውረድ ስጋት ጋር እንዲነሳ አድርጎት ነበር። ነገር ግን በፍጥነት በማገገም በቅዱስ ጊዮርጊስ 10ኛው ሳምንት ላይ እስከተሸነፈበት ሳምንት ድረስ በርካታ ድሎችን በማሳካት ከተከታታይ ሽንፈቶቹ አገግሟል። የመጀመሪያው ዙር እስኪገባደድ ድረስም በተመሳሳይ አኳኋን በመቀጠል በወቅቱ የማይቀመስ ይመስል የነበረው ደደቢትን የአሸናፊነት ጉዞም እስከመግታት መድረስ ችሏል። አባ ጅፋር ሁለተኛውን ዙር ሀዋሳ ላይ በሽንፈት መጀመሩ እንደመጀመሪያው ዙር ወደ ውጤት ማጣት እንዳይወስደው ቢያሰጋም በቀጣይ ሳምንታት ባደረጋቸው ጨዋታዎች ግን ይበልጥ ትኩረትን እየሳበ እና ድሎችን እያስመዘገበ በላይኛው የሰንጠረዡ ፉክክር መርጋት ችሏል። ሆኖም 22ኛው ሳምንት ላይ ሲደርስ ሌላ የውጤት መንሸራተት እንዲገጥመው ግድ ሆነ። በቀጣይ አራት ጨዋታዎች ወይም ከአንድ ወር በላይ ጨዋታዎችን ማሸነፍ ተስኖትም ሰነበተ። ነገር ግን እነዚህ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት የተጠናቀቁ እንጂ ሽንፈት የተመዘገባባቸው አልነበሩም።  ወደ አሸናፊነት መመለስ ሲከብዳቸው የማይታዩት አባ ጅፋሮች አሁንም ሶስት ተከታታይ ድሎችን በማስመዝገብ ውጤታቸውን አስተካክለው ሊጉን ለመምራት በቅተዋል። ምንም እንኳን 28ኛው ሳምንት ላይ በተፎካካሪያቸው ቅዱስ ጊዮርጊስ ብዙ ባገባ በሚለው ህግ ተበልጠው ሁለተኛ ደረጃን ለመያዝ ቢገደዱም የሻምፒዮንነት ተስፋቸውን ይዘው ለዛሬው ቀን በቅተዋል።በዛሬው የውድድር አመቱ የመጨረሻ ቀን ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀዋሳ ከተማን ጅማ አባ ጅፋር ደግሞ አዳማ ከተማን ያስተናግዳሉ። አዳማ እና ሀዋሳ የነጥብ ስብስባቸውን ከፍ ከማድረግ ባለፈ የተለየ ግብ የሌላቸው በመሆኑም የአሸናፊነቱ ግምት የተሰጠው ለጊዮርጊስ እና አባ ጅፋር ነው። ነገር ግን አሁን ላይ ከነጥብ ባለፈ በግብ ልዩነትም ጭምር ዕኩል ሆነው ብዙ ባገባ በሚለው ህግ የተለዩት ሁለቱ ቡድኖች ዛሬ የመጨረሻ ፈተናዎቻቸውን በድል ማጠናቀቅ ብቻ ሳይሆን በርካታ ግቦችንም ማስቆጠር ይጠበቅባቸዋል። ከቡድን ዜና ጋር በተያያዘ ምንም የቅጣት ዜና የሌለባቸው ክለቦቹ በጉዳት ረገድም ካለፉት ሳምንታት እምብዛም የተለይ ዜና አልተሰማባቸውም። በዚህም መሰረት የቅዱስ ጊዮርጊሶቹ ሰላዲን ሰይድ ፣ አማራ ማሌ እና ሪቻርድ አፒያ እንዲሁም የጅማ አባ ጅፋሮቹ ቢኒያም ሲራጅ እና አሮን አሞሀ በቡድኖቻቸው የ30ኛ ሳምንት ጨዋታ ላይ የማይገኙ ይሆናል። በዳኝነቱ በኩል ደግሞ ኢንተርናሽናል አርቢትር ብሩክ የማነ ብርሀን አዲስ አበባ ላይ ኢንተርናሽናል አርቢትር በላይ ታደሰ ጅማ ላይ በ 08፡00 የጨዋታዎቹን መጀመር እንደሚያበስሩ ይጠበቃል።በበርካታ አወዛጋቢ ጉዳዮች በታጀበው የውድድር አመት የመጨረሻ ቀን ከ2003ቱ ትዕይንት 7 ዓመታትን ተሻግረን ዘንድሮ ለሌላ የ90 ደቂቃ ትኩሳት ደርሰናል። የዘንድሮውን የሚለየው በነጥብ ብቻ ሳይሆን የግብ ልዩነታቸው ጭምር እኩል ሆነው የተገኙት ክለቦችን እጣ ፈንታ ለመመልከት መዘጋጀታችን ነው። ከ14 ዓመታት በኋላ ሁለት ቦታ ዋንጫ ተቀምጦ የሚደረገው የ30ኛ ሳምንት ማንን የዋንጫ ባለቤት ያደርግ ይሆን? ቅዱስ ጊዮርጊስን ወይስ ጅማ አባ ጅፋርን ?     ", "passage_id": "e4252fed7e374f26d8dd160c7e4a1de1" } ]
ca7271e4d9f99acc3c4b0f1c211cd069
694484fb34191456dfdb527c7e3e6706
የበጋ ወራት ውድድሮች ጠንካራ ፉክክር እያስተናገዱ ነው
ካለፈው ታኅሣሥ አጋማሽ አንስቶ እየተካሄደ የሚገኘው የሠራተኞች የበጋ ወራት የስፖርት ውድድር በጠንካራ ፉክክር ታጅቦ ቀጥሏል። በተለይም በሁለት ዲቪዚዮን ተከፍሎ የሚካሄደው የእግር ኳስ ውድድር ጠንካራ ፉክክር በማስተናገድ ላይ መሆኑን የውድድሩ አዘጋጅ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) የስፖርት ክፍል ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ካሳ ተናግረዋል። በስምንት ቡድኖች መካከል የሚካሄደው የአንደኛ ዲቪዚዮን የእግር ኳስ ውድድር ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በአራት ጨዋታ አስራ ሁለት ነጥብና አስራ ሁለት ንፁህ ግብ በመሰብሰብ እየመራ ይገኛል። የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በሦስት ጨዋታዎች በሰበሰበው ዘጠኝ ነጥብና ሰባት ንፁህ ግብ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በቅርብ ርቀት እየተከተለ ይገኛል። አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በበኩሉ በአራት ጨዋታ ዘጠን ነጥብና ስድስት የግብ ዕዳ ይዞ በሦስተኛነት ይከተላል። አዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን በሦስት ጨዋታ ሦስት ንፁህ ግብና አራት ነጥብ ይዞ ጠንካራ ፉክክር እያደረገ ይገኛል። ሸገር የብዙሃን ትራንስፖርት ከሦስት ጨዋታ ሦስት ነጥብና ሁለት የግብ ዕዳ ይዞ አምስተኛ ላይ ይገኛል። አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ በሦስት ጨዋታ አንድ ነጥብና ስምንት የግብ ዕዳ ይዞ ይከተላል። ኢትዮጵያ መድህን ድርጅትና መከላከያ ኮንስትራክሽን በሦስት ጨዋታ ስምንትና አስር የግብ ዕዳ ይዘው ካለምንም ነጥብ በአንደኛው ዲቪዚዮን እየተፎካከሩ የሚገኙ ቡድኖች ናቸው። በመጀመሪያው ዲቪዚዮን እሁድ ዕለት ሁለት ጨዋታዎች ሲካሄዱ ኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ከኢትዮጵያ መድህን በኢትዮጵያ ወጣቶች አካዳሚ የሚገናኙ ይሆናል። ቀሪው አንድ ጨዋታ በተመሳሳይ ዕለትና ቦታ አዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ከአንበሳ አውቶቡስ ጋር የሚያገናኝ ነው። በሁለተኛ ዲቪዚዮን እየተፎካከሩ የሚገኙ አስራ ስምንት ቡድኖች የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ወሳኝ ጨዋታዎችን የሚያከናውኑ ሲሆን በምድብ ‹ሀ› ከሦስት ጨዋታዎች ሙሉ ዘጠኝ ነጥብና ሦስት ንፁህ ግብ ማግኘት የቻለው ሞዔንኮ ኩባንያ እሁድ ዕለት በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ቃሊቲ ብረታብረት ፋብሪካን ይገጥማል። ቃሊቲ ብረታብረት በምድቡ ከሦስት ጨዋታዎች ሰባት ነጥብና ስድስት ንፁህ ግብ በመሰብሰብ ሦስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በዚሁ ምድብ በሦስት ጨዋታ ሰባት ነጥብና ዘጠኝ ግብ በመያዝ ሁለተኛ ላይ ይገኛል። አዋሽ ወይን ጠጅ ፋብሪካ ከኢትዮጵያ ክፍያ መንገዶች የሚያደርጉት ጨዋታም ተጠባቂ ይሆናል። ሁለቱ ቡድኖች በምድብ ‹ለ›የሚገኙ ሲሆን አዋሽ ወይን በሁለት ጨዋታ አራት ነጥብና ሁለት ግብ ይዞ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ክፍያ መንገዶች በበኩሉ በሁለት ጨዋታ አንድ ነጥብና ሁለት የግብ ዕዳ ይዞ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በዚሁ ምድብ ሦስተኛ ላይ የሚገኘው ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ካምፓኒ(ኮካ ኮላ) በሁለት ጨዋታ ሦስት ግብና አራት ነጥብ ይዞ በአራት ጨዋታ ሰባት ነጥብና አንድ ግብ ይዞ ሁለተኛ ላይ የሚገኘው አምቼ ኩባንያን ይገጥማል። ኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከረጲ ሳሙናና ዲተርጀንት፣ኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት ከ ይርጋለም አዲስ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የሚያደርጉት ጨዋታም ይጠበቃል። ከእግር ኳስ በተጨማሪ ቅዳሜ ዕለት በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት በሴቶች ቮሊ ቦል የሚካሄዱ ሦስት ጨዋታዎች የሚጠበቁ ሲሆን በተመሳሳይ ዕለት በጠረጴዛ ቴኒስ በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት የሚካሄዱ አምስት ጨዋታዎች ጠንካራ ፉክክር ያስተናግዳሉ ተብሎ ይጠበቃል። በዳርት፣ ቼስ፣ ዳማና ከረንቦላ ጨዋታዎችም የተለያዩ ፉክክሮች ይጠበቃሉ። አዲስ ዘመን የካቲት 19/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27995
[ { "passage": "ዓለምን በአንድነት እያስጨነቀ የሚገኘው ወቅታዊ ጉዳይ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ወረርሽኝ መሆኑ ይታወቃል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ያስቻለ ፈውስ በዓለም ሳይንቲስቶች፣ የህክምና ጠቢባንም ይሁን በሃያላን አገራት አቅም ማምጣት አልተቻለም። ይህም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ከመለወጥ አንስቶ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በርካታ አሉታዊ ተፅዕኖው እንዲያርፍ አድርጓል። የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ተጽዕኖ እያስተናገደ ከመሆኑ ባሻገር፤ ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጉን መረጃዎች ያመላክታሉ። በወረርሽኙ ሳቢያ ትልልቅ የስፖርት ውድድሮች በመራዘማቸው፣ በመሰረዛቸው እና በመስተጓጐላቸው ኢንዱስትሪውን ከፍተኛ ገቢ እንደሚያሳጣው የተለያዩ ትንበያዎች አመልክተዋል። \nየስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰ ርሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል፡፡ በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በዚህ ዓመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል። የስፖርት እንቅስቃሴን ጨምሮ ሌሎች መደበኛ እንቅስቃሴዎችን በቅርብ ጊዜ ማድረግ የሚቻልበት ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ምልክቶች እየታዩ አለመሆኑ፤ በኢንደስትሪው ላይ የሚደርሰው ቀውስ እንዲያሻቅብ እንደሚያደርገው ተነግሯል። \nየቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ በመሆኑ ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ጠባብ መሆኑ እየተነገረ ባለበት ወቅት ቢቢሲ ከቀናት በፊት ይዞት የወጣው መረጃ ተስፋ ሰጪ ሆኗል። ቢቢሲ ፤ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን\n የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር ሊመለሱ መሆኑን ጽፏል። ከዚህ ውስጥ ደግሞ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ግንባር ቀደም ሊሆን እንደሚችል አስነብቧል። የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ ማሳባቸውን ጠቅሶ፤ በተለይ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማጠናቀቅ ቆርጠው ተነስተዋል ሲል አስነብቧል። \nየዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን መለገሳቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ የተለያዩ ሀገራት ሊጎች እንደ አማራጭ እየቀረበ ይገኛል። በዝግ ስታዲየም ውድድሮችን አማራጭን ወደ ተግባር ለመቀየር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ቆርጠው መነሳታቸውን አስነብቧል። \nየ2020 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር የተቋረጠው። ሊጉ የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ 92 ጨዋታዎች ይቀሩታል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም የውድድር ዘመኑን በመደበኛው መልኩ ለማካሄድ ለመመለስ የሚያስችል ተስፋ የለም። የ2020 ውድድር ዘመን 92 ጨዋታዎችን እንዴት እናጠናቅ በሚለው ዙሪያ የሊጉ ክለቦች የቪድዮ ስብሰባ አድርገዋል። \nበስብሰባው ላይ እንደ ሕክምና ባለሙያዎች ያሉ ያገባቸዋል የተባሉ ሰዎችም ተገኝተው ነበር። ክለቦች ሊጉ በቀላሉ ወደ ውድድር እንደማይመለስ መግባባት ላይ ደርሰዋል። የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ የተቀሩትን ውድድሮች በዝግ ስታዲየም ለማድረግ ከስምምነት መድረሳቸውን ቢቢሲ አስነብቧል። በቪዲዮ ስብሰባ ወቅት «የሊጉ ክለቦች ይህን ለማድረግ ደግሞ ቢያንስ 10 ገለልተኛ ሜዳዎች ያስፈልጋሉ ። ገለልተኛ\n ሜዳዎችን መጠቀም ያስፈለገው ደጋፊዎች ከሜዳ ውጪም ቢሆን እንዳይሰበሰቡ በማሰብ ነው። አልፎም የሚመረጡት ሜዳዎች ከፖሊስና የስፖርት ሜዳዎችን ደህንነት ከሚመረምር አካል ይሁንታ ያገኙ መሆን አለባቸው» መባሉን በዘገባው አስፍሯል። በተጨማሪም ተጫዋቾች በሳምንት ሁለት ጊዜ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ይደርግላቸዋል። በየቀኑ ደግሞ የበሽታው ምልክት ታየባቸው አልታየባቸው የሚለው ይለካል። አልፎም ሜዳዎች በየጊዜው ንፅህናቸው ይጣራል ተብሏል። ተጫዋቾች ከጨዋታ ውጪ ባሉት ጊዜያት ሁሉ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አለባቸው። በውድድር ስፍራዎች ውስጥም ምግብ መብላትም ሆነ ገላን መታጠብ እንዳይችሉ የሚደረግ መሆኑን አመልክቷል። \nየእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማ ጠናቀቅ በገለልተኛ ሜዳ ውድድሮችን ለማድረግ ከስምምነት መድረስ ቢችሉም ከሀገሪቱ መንግስት በኩል የሚኖረውን ተቀባይነት ምን ሊሆን ይችላል ? የሚለው ምላሽ የሚያሻ መሆኑን ዘገባው አንስቷል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት እንዲቆም የተደረገው። የፕሪሚየር ሊጉ አስተዳዳሪ አካል መንግሥት ይሁንታ ሲሰጥ ብቻ ወደ ሜዳ የሚመለስ መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። \nየውድድር አመቱ የቀሩትን 92 ጨዋታዎች ለመጫወት ከስምምነት ቢደርሱም የሀገሪቱ መንግስት ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል የተባለ ነገር አለመኖሩን ዘገባው ጠቅሷል። የዚህ ዓመት ወድድር ይቋረጥ የሚል ሐሳብ ከየትኛውም ክለብ አልመጣም ነበር። በመሆኑም በሁሉም የሊጉ ክለቦች በኩል የተወሰነው ውሳኔ ከመንግስት ድጋፍ የሚያገኝ ከሆነ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መቋጫው በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ሊሆን እንደሚችል ግምቱን አስፍሯል። የእንግሊዝ መንግሥት እንቅስቃሴዎች ቀስ በቀስ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ካደረገ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በዝግ ሜዳ ወደ ውድድር እንደሚመለስ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 27/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "35430572a053b74df06f2fa400489660" }, { "passage": "ሀገር አቀፍ የትምህርት ቤቶች ውድድር በስፖርቱ እድገትና ውጤት ሁለንተናዊ ሚና እንዳለው ይታመናል። የስፖርት ፖሊሲውም ይሄንኑ መሰረት በማድረግ በትኩረት አቅጣጫው ካደረጋቸው አበይት ጉዳዮች ውስጥ ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሠራበት አካባቢ በስፖርት እንቅስቃሴ ተሳታፊ የሚሆንበት ሁኔታ እንዲሚመቻች ያትታል። በትምህርት ቤቶች ከሚደረገው ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በተጓዳኝ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስፖርታዊ ክንውን በማዘጋጀት ፍሬያማነቱን በትምህርት ቤቶች ውድድር ይመዝናል። ውድድሩ ተማሪዎች የላቀ የስፖርት ችሎታቸውን በስፖርታዊ ጨዋነት ታንፀው የሚያቀርቡበት፣ የሚታዩበትና የተሻሉት ፍላጎታቸው ከታከለበት ባሉት የሀገራችን የስፖርት አካዳሚዎች፣ ክለቦች በየስፖርት ዲስፕሊኑ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የሚታዩበትን እድል የሚፈጥር፣ ለኦሎምፒክ ራሳቸውን የሚያጩበት ትልቅ መድረክ እንደሆነ ይታመናል። ለነገይቱ ኢትዮጵያ ስፖርት ውጤት ትልቅ ተስፋ እንዳለው የሚታመነው አገር አቀፉ የትምህርት ቤቶች ውድድር ለ3ኛ ጊዜ በትግራይ ክልል አዘጋጅነት በመቀሌ ከተማ ተዘጋጅቷል። «በትምህርት ቤቶች ስፖርት ውድድር የተማሪዎችን ማህበራዊ ሰላምና ግንኙነት ማጠናከር፤ የአብሮነት ባህልን ማዳበር» በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው ሀገር አቀፍ የትምህርት ቤቶች ውድድር ለሀገሪቱ ስፖርት ውጤታማ የሆኑ ታዳጊዎች የሚታዩበት መድረክ ይሆናል የሚል ተስፋ የሰነቀ ነው። በሌላ ወገን፤ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ውድድር ተማሪዎች የላቀ የስፖርት ችሎታቸውን በስፖርታዊ ጨዋነት ታንፀው የሚያቀርቡበት ትልቅ አጋጣሚ የሚፈጥር እንደሆነ ይጠበቃል። በመሆኑም በዘንድሮ ውድድር ከምንም በላይ ስፖርታዊ ጨዋነት ችግር እንዳይፈጠር ተሳታፊ ክልልሎቸም ሆኑ አዘጋጁ ክልል ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉ ተነግሯል። ተሳታፊዎች አጋጣሚውን እንደመልካም እድል በማየት የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን የሚያጠናክሩበት ትልቅ አውድ እንደሚሆን ከስፖርታዊ ክንውኑ በተጓዳኝ የሚጠበቅ ውጤት ይሆናል። በዚህ መንፈስ ከመጋቢት 15 ቀን 2011 ዓ.ም በይፋ በመቀሌ ስታዲየም የተጀመረው ውድድር በከፍተኛ ፉክክርም እንደቀጠለ ይገኛል። እስከ ትናንት በነበረው ቆይታ የምድብና ዙር እንዲሁም የፍጻሜ ጨዋታዎች ተከናውነዋል። በሴቶች ቼስ ስፖርት የዙር ውድድር ድሬዳዋ ከአማራ ጨዋታቸውን ያከናወኑ ሲሆን የአማራ ክልል ድሬዳዋን 3ለ1 ረትቷል። በእለቱ የተከናወነው ሌላው የቮሊቦል ጨዋታ ነበር። በቮሊቦል የምድብ ውድድር በወንዶች ኦሮሚያ ከደቡብ ተገናኝተው ደቡብ 3ለ1 በሆነ ውጤት ኦሮሚያን ረትቷል። ትግራይ ሀረሪን 3ለ0 ሲያሸንፍ፤ አዲስ አበባ አማራን 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ጋምቤላ ከአፋር ክልል ጋር ባደረገው ጨዋታ ጋምቤላ በጨዋታ ብልጫ ጭምር 3 ለ0 በመርታት የምድብ ጨዋታቸውን በድል ጀምረዋል። በውድድሩ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የሴቶቸ እግር ኳስ አማራና ተግራይን ያገናኘ ሲሆን፤ አዘጋጁ ክልል የ3ለ1 ሽንፈት ደርሶበታል። በወንዶች የቅርጫት ኳስ ውድድር አዲስ አበባ ከደቡብ ያደረጉት ጨዋታ በእጅጉ ትኩረት የሳበ ነበር። ብርቱ ፍክክር በታየበት በዚህ ጨዋታ አዲስ አበባ ደቡብን 39 ለ 52 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በተመሳሳይ፤ አማራ ከሀረሪ 28 ለ 39፣ ጋምቤላ ከትግራይ 41 ለ 53፣ ኦሮሚያ ከድሬዳዋ 44 ለ 28 በሆነ ውጤት አሸናፊ ሆነዋል። በአትሌቲክስ፤ የወንዶች ርዝመት ዝላይ ኦሮሚያ 1 እና 3ኛ ደረጃን ሲይዝ ፣ትግራይ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ማሸነፍ ችለዋል። በ100 ሜትር ወንድ አማራ፣ ኦሮሚያ እና ደቡብ ከ1 እስከ 3 ያለውን ደረጃ ሲይዙ በሴቶች አማራ 1ኛ እና 3ኛ ደረጃ በመያዝ ሲያሸንፍ፤ ኦሮሚያ 2ኛ ደረጃ አግኝቷል። በሴቶች ኦሮሚያ 1ኛ እና 2ኛ ሲይዙ፤ ትግራይ 3ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቅቋል። በ800 ሜትር ወንዶች ኦሮሚያ፣ አማራ እና ትግራይ ከ1 እስከ 3 ያለውን ደረጃ ሲይዙ፤ በሴቶች ኦሮሚያ አሸናፊ ሲሆን የትግራይ ተወዳዳሪዎች 2ኛ እና 3ኛ ሆነዋል። በዲስከስ ውርወራ ሴቶች፤ ኦሮሚያ1ኛ ሲወጣ አማራ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ይዞ ሲያጠናቀቅ፤ በ110 ሜትር መሰናክል ወንዶች አማራ አሸናፊ ሲሆን፤ ኦሮሚያ 2ኛ 3ኛ ደረጃ ይዟል።በዝግጅቱ ፍጻሜያቸውን ያገኙ ውድድሮች ሲኖሩ፤ አትሌቲክስ የፍፃሜ ውድድር በ5000 ሜትር ወንዶች ኦሮሚያ ወርቅ፣ ትግራይ የብርና ነሀስ ፣ ስሉስ ዝላይ ኦሮሚያ የወርቅ፣ ትግራይ የብር፣ አማራ የነሀስ ሜዳሊያ ማሸነፍ ችለዋል። በአሎሎ ውርወራ ሴቶች ኦሮሚያ የወርቅ፣ የብርና የነሀስ ተሸላሚ ሲሆኑ በ3000 ሜትር አማራ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ሲሆን፤ ትግራይ የብርና የነሀስ ተሸላሚ ሆኗል። በሴቶች ርዝመት ዝላይ ውድድር አማራ ወርቅ፣ ኦሮሚያ ብርና ነሀስ አሸናፊ ሆነዋል። በሴቶች ብስክሌት የግል ክርኖ ውድድር ትግራይ የወርቅ እና የብር፣ አማራ የነሃስ ሜዳሊያ አሸናፊ ሲሆኑ፤ በወንዶች አዲስ አበባ የወርቅ ፣ ትግራይ የብር እና የነሃስ ተሸላሚ ሆነዋል።በመቀለ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው 3ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ቤቶች ውድድር እስከ መጋቢት 28 ቀን 2011 ዓ.ም ይቀጥላል። በውድድሩ ሰባት ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች የሚሳተፉ ሲሆን፤ አማራ 565፤ ኦሮሚያ 507፤ አዲስ አበባ 650፤ ድሬዳዋ 239፤ ደቡብ 405፤ ሀረሪ 107፤ አፋር 79 ፤ ጋምቤላ 128 እና አዘጋጁ ትግራይ ክልል 473 የስፖርት ልዑካንን እያሳተፉ ይገኛሉ። የሶማሌና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በበጀት ችግር ምክንያት በዚህ ውድድር አልተሳተፉም።አዲስ ዘመን መጋቢት 18/2011በ ዳንኤል ዘነበ –", "passage_id": "c64435bd8c41fe676bac5fc131ad5a49" }, { "passage": " እየተጋመሰ የሚገኘው የሚያዝያ ወር በዓለም ላይ በርካታ የጎዳናና የማራቶን ውድድሮች የሚስተናገዱበት ነው። ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ በሰጣቸው የተለያዩ ውድድሮች ከፍተኛ ድል በማስመዝገብ ገፍተውበታል። ባሳለፍነው ሳምንት እንኳን ፓሪስና ቦስተን ማራቶኖች ላይ አስደናቂ ድሎችን በማስመዝገብ የረጅም ርቀት ኮከብነታቸውን ለዓለም ማሳየት ችለዋል። ዛሬና ነገ በሚካሄዱ የማራቶንና የግማሽ ማራቶን ዓለም አቀፍ ውድድሮችም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከወዲሁ ለድል ታጭተዋል። የወርቅ ደረጃ የተሰጠው ዶንግዪንግ ዓለም አቀፍ ማራቶን ዛሬ ሲካሄድ በሁለቱም ፆታ የቦታው ክብረወሰን ይሻሻላል ተብሎ ይጠበቃል። በውድድሩ በተለይም በሴቶች ከዚህ ቀደም አሸናፊ የነበረችው ዋጋነሽ መካሻ ዳግም ለአሸናፊነት መታጨቷን አዘጋጆቹን ጠቅሶ አይ.ኤኤ.ኤፍ በድረ ገፁ አስነብቧል።ባለፈው ጥር ወር በዱባይ ማራቶን አራተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ 2:22:45 የሆነ የግል ምርጥ ሰዓቷን በማራቶን ያስመዘገበችው ዋጋነሽ በርቀቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተስፋ ከሚጣልባቸው ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አንዷ ነች። የመጀመሪያ የማራቶን ውድድሯን እአአ 2014 ሲንጋፖር ላይ ካደረገች ወዲህ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየች የምትገኘው የ27 ዓመቷ አትሌት፣ ባለፈው ዓመት በቻይና ሄንግሹ ያሸነፈችበትን ውድድር ጨምሮ በአራት ውድድሮች የተሻለ ሰዓት እያስመዘገበች መምጣቷ በዛሬው ውድድር ከአሸናፊነት ባለፈ ክብረወሰን ለማሻሻል አቅም እንዳላት እምነት ተጥሎባታል። ባለፈው ዓመት በለተብርሃን ሃይላይ የተመዘገበው 2:24:45የውድድሩ ክብረወሰን ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ከኬንያውያን ተፎካካሪዎቿ ጋር ልታሻሽለው ትችላለች ተብሎ ይጠበቃል።ለዚህም በውድድሩ የመጀመሪያውን ፈጣን ሰዓት የያዘችው ኬንያዊት ካሮሊን ቼፕታኑይ ያላት ጥንካሬ ፈጣን ሰዓት ሊመዘገብ እንደሚችል ማሳያ ተደርጓል። ይህች አትሌት 2:22:34 የሆነ ግል ፈጣን ሰዓት በርቀቱ ማስመዝገብ የቻለች ሲሆን፣ እአአ 2013 በፍራንክፈርት ማራቶን ባሸነፈችበት ውድድር ነበር ሰዓቱን ያስመዘገበችው። የ38 ዓመቷ ኬንያዊት እአአ 2016 የዴጉ ማራቶንን 2:27:39 በሆነ ሰዓት ካሸነፈች ወዲህ ባደረገቻቸው ውድድሮች ርቀቱን ከ2፡30 በታች ማጠናቀቅ አልቻለችም። ባለፈው ዓመትም በዚሁ ዶንግዪንግ ማራቶን አምስተኛ ሆና ስትፈፅም ማስመዝገብ የቻለችው ሰዓት 2፡34፡39 ነው።ይህም የአሸናፊነቱ ግምት ወደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት እንዲያደላ አድርጓል። ከዚህ ውድድር ክብረወሰን የተሻለ የራሷ ፈጣን ሰዓት ያላት ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አፈራ ጎደፋይ ለአሸናፊነት ከታጩ አትሌቶች መካከል ተካታለች። የ27 ዓመቷ አትሌት ባለፈው ዓመት በሻንጋይ ማራቶን አራተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ቀድሞ በርቀቱ የነበራትን ፈጣን ሰዓት ከአምስት ደቂቃ ባላነሰ በማሻሻል\n2:23:54 ማስመዝገቧ ይታወሳል። በዚሁ ውድድር በወንዶች መካከል የሚኖረው ፉክክር በኢትዮጵያዊው ግርማይ ብርሃኑ አሸናፊነት እንደሚደመደም ይጠበቃል። እአአ 2014 ዱባይ ማራቶን ላይ ሦስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡05፡49 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያስመዘገበው የ32 ዓመቱ ግርማይ የዴጉ ማራቶንን ባሸነፈበት ውድድር ተቀራራቢ የሆነ 2፡07፡26 ሰዓት አስመዝግቧል። የቀድሞው የራባት ማራቶን ሻምፒዮን ፍቃዱ ከበደም ባለፈው የዱባይ ማራቶን የራሱን ምርጥ ሰዓት በሰባ ሰከንድ አሻሽሎ\n2:08:27 ማጠናቀቁን ተከትሎ ለአሸናፊነት ይጠበቃል።በዚሁ በቻይና የወርቅ ደረጃ ተሰጥቶት ነገ በሚካሄደው ያንግዞ ዓለም አቀፍ ማራቶን የቀድሞ የውድድሩ ሻምፒዮን የሆነች ኢትዮጵያዊቷ ሱቱሜ አሰፋ የአሸናፊነት ግምት አግኝታለች።\n2017 ላይ የዚህ ውድድር አሸናፊ የነበረችው የ24 ዓመቷ ሱቱሜ ከሁለት ዓመት በፊት ለድል ስትበቃ 1፡10፡30 በሆነ ሰዓት አጠናቃለች። ባለፈው የሚላን ግማሽ ማራቶን ውድድር የራሷን ምርጥ ሰዓት ወደ 1፡07፡54 ማሻሻሏ ይታወሳል። በዚህ ውድድር ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ደጊቱ አዝመራው ቀላል ግምት የሚሰጣት አትሌት አይደለችም። የ20 ዓመቷ ደጊቱ በዚህ ዓመት ገና በመጀመሪያዋ የግማሽ ማራቶን ውድድር\n1:06:47 ሰዓት በማስመዝገብ ጥንካሬዋን ማሳየት ችላለች። ከሁለት ወራት በፊትም በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የራክ ግማሽ ማራቶን ውድድር አራተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ሰዓቷን ወደ1:06:07 አሻሽላለች። የዚህ ውድድር የአራት ጊዜ አሸናፊው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሞስነት ገረመው በሌለበት የዘንድሮው ውድድር ትውልደ ኬንያዊው የባህሬን አትሌት አብረሃም ቺሮበን የአሸናፊነት ግምት ወስዷል። ቺሮበን በነገው ውድድር እአአ 2015 በሞስነት ገረመው 59፡52 ሰዓት ተይዞ የቆየውን የቦታውን ክብረወሰን ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል። ቺሮበን ባለፈው ዓመት በውድድሩ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁም አይዘነጋም።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 12/2011 ", "passage_id": "5c796f4cfdda948382c981eb2d1363d0" }, { "passage": "የአየሩ ብክለት መርዛማ ደረጃ ደርሷል በተባለለትና ትምህርት ቤቶች እስኪዘጉ ምክንያት በሆነው በዚህ የአየር ብክለት ምክንያት ውድድሩ ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ አንዳንድ የህክምና ባለሙያዎች ጠይቀው ነበር። \n\nሆኖም ውድድሩ በተካሄደበት ወቅት የነበረው አየር 'አደገኛ' ከሚል ደረጃ ወርዶ 'ለጤና የማይስማማ' በሚል ደረጃ በተቀመጠበት ወቅት ነው የተካሄደው። በውድድሩ ብርሃኑ ለገሰ በወንዶች አልማዝ አያና ደግሞ በሴቶች ቀዳሚ ሆነው መግባት ችለዋል።\n\n ከውድድሩ በፊት ብርሃኑ አትሌቶቹ 'ፈርተው እንደነበር' ገልጾ በውድድሩ ቀን የነበረው ሁኔታ ግን 'መጥፎ አለመሆኑን' ጠቅሷል። \n\nበከተሞች በሚካሄዱ ውድድሮች ላይ የሚሳተፉ አትሌቶችም ሆኑ ሌሎች ተሳታፊዎች የአየር ብክለት ሊያሰጋቸው ይገባል? \n\nምንም አዲስ ነገር የለም\n\nየአየር ብክለት ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ በስፖርታዊ ወድድሮች ላይ ስጋት እየፈጠሩ ነው።\n\n እ.አ.አ በ1984 የተካሄደው የሎስ አንጀለስ ኦሎምፒክ በአየር ብክለት ምክንያት ሌላ ጊዜ መካሄድ ነበረበት የሚሉ ነበሩ። የቻይና ባለስልጣናት ፋብሪካዎችን ዘግተው መኪኖችን ቢያግዱም፤ የ2008ቱ የቤጂንግ ኦሎምፒክ ደግሞ በውድድሩ ታሪክ ከፍተኛ ብክለት ያጋጠመበት ነበር። \n\nበነዋሪዎች ቁጥር መጨመር እና አየርን በሚበክሉ የተለያዩ ምክንያቶች በብዙ ከተሞች ያለው አየር እየተበከለ ይገኛል። \n\nአትሌቶች ለአነስተኛ ጊዜ በጣም በተበከለ አየር ውስጥ ቢወዳደሩ በጤናቸው ላይ የሚያስከትለው የረዥም ጊዜ ጉዳት ላይ ከድምዳሜ አልተደረሰም። \n\nዋናው ችግር በተበከለው አየር ውስጥ ለሚኖሩት ዜጎችነው። \n\nእንደዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ከሆነ በአየር ብክለት ምክንያት በየዓመቱ ሶስት ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸውን ያጣሉ። እንቅስቃሴ ማድረግ የምንስበውን የአየር መጠን ከፍ የሚያደርገው ሲሆን ከፍተኛ ብክለት ባለባችው አካባቢዎች ደግሞ ይህ ችግር የበዛ ይሆናል። \n\nበአዲስ አበባ የሚገኘው የአየር ብክለት ሁኔታ 'መካከለኛ' የሚባል ነው። \n\nበኢትዮጵያ ስላለው የአየር ብክለት ያለው ሳይንሳዊ መረጃ ትንሽ ነው። ሆኖም ተመራማሪዎች በምስራቅ አፍሪካ ለሚከሰተው ያለዕድሜ ሞት ትልቅ ምክንያት ነው ይላሉ። \n\nበዓለም አቀፍ ደረጃ በምስራቅ አፍሪካ ስላለው የአየር ብክለት በሚደረገው ጥናት ውስጥ አዲስ አበባ ተካታለች። ጥናቱ እ.አ.አ ከ2015 እስከ 2030 ባለው ጊዜ የከተማዋ ነዋሪ ቁጥር በ80 በመቶ ስለሚያድግ መንግሥት እርምጃ መውሰድ እንደሚገባው ለማሳሳብ ነው።\n\nብዙ ሰዎች ምግባቸውን ለማብሰል ከሰል የሚጠቀሙ ሲሆን ቆሻሻ በየመንገዱ ከመቃጠሉም በላይ የመኪኖች ቁጥር እያደገ ነው። \n\nአዲስ አበባ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ያለው የክትትል ቡድን ባለፈው አርብ የከተማዋን የአየር ሁኔታ 'መካከለኛ' ሲል አስቀምጧል። በዚህ ደረጃ መሠረት ህጻናት፣ ታዳጊዎችና የመተንፈሻ ችግር ያለባቸው ሰዎች ለረዥም ሰዓት ከቤት ውጭ ማሳለፍ አይገባቸውም። \n\nየልምምድ ቦታዎች\n\nብዙ ታዋቂ እና ጀማሪ አትሌቶች ባለው የልምምድ መሠረተ ልማት ምክንያት መሠረታቸውን በአዲስ አበባ በማድረግ እየተለማመዱ ይገኛሉ። \n\nየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ኃላፊ ሃይሌ ገብረስላሴ ችግሩ መኖሩን ገልጾ ጎጂ መሆኑን ይጠቅሳል። \n\nየቀድሞው የኦሎምፒክ ሻምፒዮን በቅርቡ አትሌቶች በአየር ብክለት ምክንያት ጉዳት እንዳይደርስባቸው ከአዲስ አበባ ውጭ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል። \n\nያለፈው ዓመት የቦስተን ማራቶን አሸናፊው ለሚ ብርሃኑ ግን የብክለቱ ችግር አነስተኛ ነው ሲል ይገልጻል። \n\n\"ስለ አየር ብክለት አናውቅም። አሰልጣኞቻችንም ስለዚህ ጉዳይ አይነግሩንም።\"\n\nዋናው ትኩረት በእርጥበት፣ የሙቀት መጠን፣ ከፍታ እና በተለያዩ የአየር ንብረቶች በመወዳደር... ", "passage_id": "ad8e30cc9f6574f8d6928f211e4af340" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳበኮቪድ 19 ወረርሽኝ እና በፈረንጆቹ የክረምት ወራት ምክንያት የአትሌቲክስ ውድድሮች ሳይካሄዱ ቆይተዋል።አሁን ግን የዓለም አትሌቲክስ እውቅናና ደረጃ የሰጣቸው ዓመታዊ ውድድሮች በያዙት መርሃ ግብር መሰረት የሚካሄዱ መሆኑን የዓለምን የአትሌቲክስ የሚመራው አካል አስታውቋል። በዚህም መሰረት በተቋሙ የፕላቲኒየም፣ ወርቅ፣ ብር እና ነሐስ ደረጃ የተሰጣቸው 191 ውድድሮች በ49 አገራት ውስጥ የሚካሄዱ ይሆናል።ከእነዚህ መካከል 168 የሚሆኑት በመርሃ ግብሩ መሰረት እንደሚካሄዱ የውድድሩ አዘጋጆች ማረጋገጫቸውን ቢሰጡም በዓመቱ በሚኖረው የወረርሽኝ መጠን እንዲሁም ሌሎች ምክንያቶች ይህ ቁጥር ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችልም ይጠበቃል። የአትሌቲክስ ስፖርትን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚመራው ተቋም የትኛውም አህጉርና ዓለም አቀፍ ውድድር ከመካሄዱ አስቀድሞ ደረጃ እና ፈቃድ ይሰጣቸዋል።በውድድር ዝግጅታቸው፣ በሚያሳትፏቸው አትሌቶች ጥራት፣ በሽልማት ገንዘባቸው፣… እንዲሁም ትልልቅ ደረጃ የሚሰጣቸው እነዚህ የአትሌቲክስ ውድድሮች የዓመቱን መርሃ ግብራቸውን በተያዘው ወር መጨረሻ የሚጀምሩም ይሆናል። የመጀመሪያው ውድድር የሚሆነውም ዘንድሮ ኦሊምፒክን በምታዘጋጀው ጃፓን በሴቶች የሚካሄድ ማራቶን ነው።ውድድሩ በኦሳካ የሚካሄድ ሲሆን፤ ከ11 ወራት በኋላ በነሐሴ የመጨረሻው ዕለት (እ.ኤ.አ 2022 አዲስ ዓመት ዋዜማ) ደግሞ በማድሪድ፣ ቦልዛኖ እና ሳኦ ፖሎ በሚካሄዱት ውድድሮች የዓመቱ መርሃ ግብር እንደሚጠናቀቅም ነው የተጠቆመው። በዓለም አትሌቲክስ ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት ጆን ሪጎን የጎዳና ላይ ሩጫዎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሯጮችን የሚያስተናግዱ እንደመሆናቸው በወረርሽኙ ምክንያት ውድድሮችን ማካሄድ ሳይችሉ መቆየታቸውን ይገልፃሉ።አሁን ግን ለአትሌቶች የገቢ ምንጫቸው እንዲያድግ እንዲሁም በውድድር ምክንያት ተሳታፊዎች ተመርምረው ራሳቸውን ከቫይረሱ ነፃ እንዲያደርጉ ማረጋገጥን ለማበረታታት ሲባል ወደ ውድድር መገባቱን ያብራራሉ። የዓለም አትሌቲክስ መስፈርቶቹን ላሟሉ ውድድሮች ደረጃ ከመስጠቱም ባሻገር በየደረጃው ባሉ የውድድር አሸናፊዎች በሽልማት ሊበረከትላቸው የሚገባ የገንዘብ መጠንንም ያስቀምጣል።በዚህም መሰረት በማራቶን ውድድር ላይ አሸናፊ ለሚሆን አትሌት 1 ሺህ 500 የአሜሪካ ዶላር በሌሎች የመም ውድድሮች በቀዳሚነት ለሚያጠናቅቅ ደግሞ 7 ሺህ 500 ዶላር እንዲበረከትላቸው ያዛል።ይህ በሁለቱም ፆታ ተመሳሳይ ሲሆን እስከ ስምንት ባለው ደረጃ ሆነው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሚያገኙት የገንዘብ መጠንም ተዘርዝሯል። ይህንን ተከትሎም ትልልቅ የጎዳና ላይ ውድድሮች መግለጫዎችን በመስጠት ላይ ይገኛሉ።በቫይረሱ ስጋት ምክንያት ባለፈው ዓመት ሳይካሄድ የቀረው የለንደን ማራቶን በዚህ ዓመት በዓለም የሩጫ ተሳታፊዎች ክብረወሰን ሊሰብር የሚችል ቁጥር ለማስመዝገብ ማቀዱንም ዘ ጋርዲያን በድረገፁ አስነብቧል። በዓመቱ አጋማሽ የሚካሄደውና በዓለም ላይ ካሉ ትልልቅ ስም ያላቸው ማራቶኖች መካከል የሚጠቀሰው ይህ የለንደን ማራቶን ከ100 ሺህ ሯጮች በሁለት ቦታ በመክፈል በተለያዩ አቅጣጫዎች የተቀሩትን ደግሞ በቴክኖሎጂ እገዛ ለማወዳደር አቅዷል። ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ሯጭ በማሳተፍ በታሪክ ቀዳሚነቱን የያዘው የኒው ዮርክ ማራቶን ሲሆን፤ እ.ኤ.አ በ2018 ተካፋይ የነበሩት ሯጮች 53 ሺህ 121 ነበሩ።የለንደን ማራቶን ዳይሬክተር የሆኑት ሃፍ ብራሸር በዚህ ዓለም ከገባችበት አስቸጋሪ ሁኔታ በቅጡ ባልተላቀቀችበት ወቅት ይህንን ያህል ቁጥር ሯጭ ለማሳተፍ የታቀደው ‹‹በወረርሽኙ ምክንያት በአትሌቲክሱ ላይ ያጠላውን ጥላ በብርሃንና ተስፋ ለመተካት ነው›› ሲሉ ይገልፃሉ።ከዚህም ባሻገር የበጎ አድራጎትና ሌሎች አካታች መርሃ ግብሮችም መታቀዳቸውን ነው የሚጠቁሙት። ዳይሬክተሩ አክለውም ‹‹ውድድሮች ከተዘጉ ዓመት ቢሆናቸውም አሁንም ድረስ በቫይረሱ ስለሚሞቱ ተጠቂዎች እየተነገረ በመሆኑ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ተሳታፊ ውድድር ስለማካሄድ መግለጽ ከባድ መሆኑ ግልጽ ነው።ነገር ግን ለውድድሩ አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ አድርገናል፤ ከዚህ ባሻገር እስካሁን በእንግሊዝ አራት ሚሊየን የሚሆኑ ሰዎች ክትባቱን በመውሰዳቸውና ውድድሩ እስከሚካሄድበት ወቅትም ቁጥሩ ስለሚጨምር በመንግሥት ፈቃድ አግኝተናል›› ሲሉም ነው ያብራሩት።", "passage_id": "92c711145089b9052afd8fb599e50094" } ]
d211199815327bf1f1a13ef128808eb6
f09ec51d75140a7e9ad31d454512eed4
የአዲስ አበባ ኢትዮ ዩናይትድ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ተመሰረተ
ምስረታውን በ1985ዓም ያደረገው ኢትዮ ዩናይትድ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለው መከፋፈል መሰረት በኢትዮጵያም በሶስት አሶሴሽኖች ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። በኢትዮጵያ በተለይ በወጣቱ ዘንድ እጅግ ከተስፋፉ ስፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው ይህ የማርሻል አርት ስፖርት በፌዴሬሽን ደረጃ ለመደራጀትም ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን 2003ዓ.ም በወጣው የስፖርት ማህበራት ማቋቋሚያ መመሪያ መሰረትም የድሬዳዋ ኢትዮ ዩናይትድ ኢንተር ናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ሊመሰረት ችሏል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ስር የነበሩት ሶስት አሶሴሽኖችም በመጣመር ፌዴሬሽን ያቋቋመ ሁለተኛው ከተማ አስተዳደር ሆኗል። በፌዴሬሽኑ ማቋቋሚያ ጉባኤ ላይም የስፖርት ኮሚሽኑ ተወካይ አቶ መኮንን ገብረህይወት የፌዴሬሽኑን ምስረታ አብስረዋል። ተወካዩ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የአሰራር ሂደቱንና ደንቡን በተከተለ መልኩ የፌዴሬሽን ምስረታ መካሄዱን አረጋግጠዋል። ፌዴሬሽኑ በስድስት ክፍለ ከተሞች ውስጥ ብቃታቸው የተረጋገጠ 16 ክለቦችን ያቀፈ፣ በ ‹‹ኤ ላይሰንስ›› ሁለት፣ በ ‹‹ቢ ላይሰንስ›› ስድስት፣ በ ‹‹ሲ ላይሰንስ›› አስር ዳኞች እንዲሁም ከ2-7ኛ ዳን ያላቸው 16 አሰልጣኞች ያሉት በመሆኑ የማቋቋሚያ ጉባኤ ማድረግ የሚያስችላቸው መሆኑን ጠቁመዋል። በዚሁም መሰረት ስራ አስፈጻሚዎችን በመምረጥ ወደ ስራ እንዲገቡ፤ በሂደትም ጽህፈት ቤትና የስፖርት ማዘውተሪያ ገንብተው ከመንግስት ድጎማ እስኪላቀቁ በኮሚሽኑ ቢሮ እንዲሁም በትምህርትና ስልጠና ማዕከላት እንዲገለገሉ ፈቃድ ተሰጥቷል። በመጀመሪያው ጉባኤ ላይም አዲስ ፌዴሬሽን እንደመሆኑ ሪፖርት ማቅረብ ባይቻልም ቀጣይ እቅዶች ግን ለጉባየተኛው ቀርበዋል። በዚህም የክለቦችን ቁጥር አሁን ካለበት ቁጥር ወደ 33 ማሳደግ፣ ጠንካራ ፌዴሬሽን እንዲሆን መስራት፣ ገቢውን በማሳደግ ከኮሚሽኑ ድጋፍ የሚላቀቅበትን መሰረት መጣል፣ የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላትን ማሳደግ፣ ስፖርተኞችን በሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ማሳተፍ፣ የተለያዩ ቻምፒዮናዎችን በማዘጋጀት ከተማ አስተዳደሩን እንዲሁም ሀገርን ለመወከል የሚችሉ ስፖርተኞችን ማፍራት፣ በትምህርትና ስልጠና የዳኞችንና አሰልጣኞችን ቁጥር ወደ 100 ማሳደግ እንዲሁም በክትትልና ድጋፍ ላይ ለመስራት መታቀዱ ተገልጿል። ገለጻውን ያዳመጠው ጉባኤም በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። በመተዳደሪያ ደንቡ ላይም ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ በጉባኤው አባላት ይሁንታ ሊያገኝ ችሏል።ከተሳታፊዎች በተሰጠው አስተያየትም ስፖርቱ እስከ ወረዳ በመውረድ በይበልጥ እንዲስፋፋ ፌዴሬሽኑ ከክፍለ ከተሞች ጋር በቅንጅት መስራት እንዳለበት እና ከመንግስት ድጎማ ለመላቀቅ የሚያስችለውን መንገድ ማፈላለግ እንዲሁም የሀብት አሰባሰብ ላይ ማተኮር እንደሚገባው ተጠቁሟል። በተካሄደው የስራ አስፈጻሚዎች ምርጫም አቶ በቀለ በዳዳ በ14 ድምጽ በማሸነፋቸው ከቀድሞው የአሶሴሽኑ ፕሬዚዳንት ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሲኒየር ሳቦም ተሾመ አበበ የስራ ደንብና መመሪያ ተረክበዋል። አቶ መንሱር ጀማል ምክትል ፕሬዚደንት ሲሆኑ፤ ወይዘሮ ሰብለወንጌል ቁምላቸው አቃቤ ነዋይ እንዲሁም ሌሎች አራት ግለሰቦች የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በመሆን ተመርጠዋል። ተመራጮችም በጋራ በመሆን ስፖርቱን ለማሳደግ የሚሰሩ መሆኑን ቃል ገብተዋል። ከማርሻል አርት ስፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ እአአ 1966 በጄኔራል ቾይ ሆንግ ሃይ ነው የተመሰረተው። የሁለቱን ኮሪያዎች መነጣጠል ተከትሎም ኢንተርናሽናልና ወርልድ ቴኳንዶ በሚል ሲከፈል፤ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ በሰሜን ኮሪያ በስፋት ይከወናል። በሲኒየር ማስተር አብዲ ከድር መስራችነትም በኢትዮጵያ አሶሴሽኑ እስካሁን ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። በዚህ ወቅት የዓለም አቀፉ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን መቀመጫ በኦስትሪያ ቬና ሲሆን፤ ኢትዮጵያም አባል አገር ናት።አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 21/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28137
[ { "passage": "በመጋቢት 2009 የተመረቀው የይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚን እንዲያስተዳድሩለት የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር የተለያዩ የአውሮፓ ሃገራት የእግርኳስ አካዳሚዎችን ካወዳደረ በኃላ ከስፔኑ ሶክስና የእግርኳስ ማህበር ጋር ዛሬ በሸራተን አዲስ የመግባቢያ ሰነድ ውል ተፈራርሟል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለሶክስና የአምስት ዓመት ውል የሰጠ ሲሆን 50 ለሚሆኑ ታዳጊዎች ስልጠናውን በመስጠት ማዕከሉ ወደ ስራ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡ቅዱስ ጊዮርጊስን፣ ሶክስና እና ኢ ፎር ኢ የተባለ የስፔን ድርጅቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያማክር ድርጅት የመግባቢያ ሰነዱን ዛሬ ፈርመዋል፡፡ በፊርማው ስነ-ስርዓት የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ ፕሬዝደንት አቶ አብነት ገብረመስቀል እንደተናገሩት የእግርኳስ አካዳሚ መገንባት የክለባቸው የረጅም ግዜ ምኞት እንደነበር ገልፀዋል፡፡ “ ለኢትዮጵያው ቀደምት ክለብ የወጣቶች አካዳሚ መገንባት ሁሌም ህልማችን ነበር፡፡ ይህ ምሽት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ታሪካዊ ነው፡፡ ምክንያቱም አካዳሚያችንን ሶክስና እንዲያስተዳድረው የተስማማንበት እለት ስለሆነ፡፡ ይህ ለኢትዮጵያዊያን ታዳጊዎች ወሳኝ የሆነ ኢንቨስትመንት ነው፡፡ በስፔን እና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን ጠንካራ ግንኙነትም የሚያስቀጥል ነው፡፡” ብለዋል፡፡የሶክስና የእግርኳስ ማዕከል ምክትል ፕሬዝደንት ዴቪድ ሎፔዝ በበኩላቸው ውሉ የተሳካ እንዲሆን ያስቻሏቸውን አካላት አመስግነዋል፡፡ “በዚህ ጥሩ ግዜ በመገኘቴ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ ሶክስና የእግርኳስ አስተዳደር ድርጅት ነው፡፡ በስፔን፣ ቻይና እና ሆንግ ኮንግ ቢሮዎች ያሉን ሲሆን አሁን በቅርቡ በኢትዮጵያም ይኖረናል፡፡ ድርጅታችን በታዳጊዎች ስልጠና ፕሮግራሞች ላይ በልዩነት የሚሰራ ነው፡፡ ለእኛ በኢትዮጵያው ምርጥ ክለብ እንዲሁም በአፍሪካ ከምርጥ ክለቦች ተርታ በሚመደበው ቅዱስ ጊዮርጊስ መመረጥ መቻላችን ትልቅ ክብር ነው፡፡ የዚህ አስገራሚ ፕሮጀክት አካል እንድንሆን ያስቻሉንን ሁሉ ማመስገን እፈልጋለው፡፡ ተስጥኦ ሁሉም ቦታ አለ፤ በኢትዮጵያም ተፈልጎ ለመገኘት የሚገባው ብዙ ተስጥኦ እንዳለ እናምናለን፡፡ የእኛም የመጀመሪያ ስራ እነኚህን ተስጥኦ ያላቸው ታዳጊዎች ከሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ከኢትዮጵያዊያን አሰልጣኞች ጋር በመሆን የመለየት ስራ ነው፡፡ ለቅዱስ ጊዮርጊስ አካዳሚ የሚሆን የአምስት አመት ስትራቴጂም የምንቀርፅ ነው የሚሆነው፡፡”ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሶክስና እንዲገናኙ ከፍተኛውን ሚና የተጫወተው የስፔኑ ኢንቨስትመንት አማካሪ ድርጅት የሆነው ኢ ፎር ኢ ሲሆን የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሁሊዮ ፓዞ  በንግግራቸው ቅዱስ ጊዮርጊስ ለታዳጊዎች ስልጠና የሚረዳውን አጋር ድርጅት ይፈልግ እንደነበረ ጠቁመው ሶክስና ለዚሁ ብቁ ሆኖ በመገኘቱ ይህ ውል ሊፈፀም እንደቻለ አስረድትዋል፡፡በማድሪድ የእግርኳስ ማዕከል ያለው ሶክስና በቻይና የጉዋንዡ ኤቨርንግራንዴ ክለብን አካዳሚን ማስተዳደር ሲችል በአፍሪካ የታዳጊዎች ስልጠና ፕሮግራም ላይ ሲሳተፍ ይህ ለመጀመሪያ ግዜ ነው፡፡ ለ50 ታዳጊዎች ስልጠናው የሚሰጥ ሲሆን በመጀመሪያው አመት 359ሺ ዩሮ ወጪ ይደረጋል፡፡ በሁለተኛው አመት ወጪው ጨምሮ 679ሺ ዩሮ የሚሆን ሲሆን እንደአካዳሚው የቅበላ አቅም ወጪው እየጨመረ እንደሚመጣ ይጠበቃል፡፡ ከአምስት አመት በኃላ የእውቀት ሽግግር ተደርጎ ኢትዮጵዊያን ባለሙያዎች አካዳሚውን እንዲመሩ እንደሚፈልግ አቶ አብነት ተናግረዋል፡፡ በአካዳሚው እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ዋና ቡድን መካከል ስለሚኖረው ግንኙት የሶክስና እና የስፖርት ማህበሩ ውይይት እንደሚያደርጉ ሎፔዝ ጨምረው ገልፀዋል፡፡(ከሶክስና ምክትል ፕሬዝደንት ዴቪድ ሎፔዝ እና ኢ ፎር ኢ ዋና ስራ አስኪያጅ ሁሊዮ ፓዞ ለጋዜጠኞች ስለውሉ እና ተያያዥ ጉዳዮች የሰጡትን ሰፋ ያለ አስተያየት አርብ ይዘን እንመለሳለን፡፡)", "passage_id": "af54f753a1831405052d5ca365f37cbb" }, { "passage": "ከሰባት ዓመት በፊት የተጀመረው የከተሞች የቅርጫት ኳስ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ከተሞች በድምቀት ሲካሄድ ቆይቷል፡፡ ከአንድ ዓመት መቋረጥ በስተቀር ውድድሩ የተካሄደ ሲሆን ዘንድሮ ለስድስተኛ ጊዜ በቢሾፍቱ ከተማ ‹ጎሲ ስፖርት ማዕከል› ውስጥ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በወንድ ስድስትና በሴት ሁለት ከተሞችን እያሳተፈ የሚገኘው ይህ ውድድር ባለፈው እሁድ ተመጣጣኝ ፉክክር ባስተናገደው የቢሾፍቱና ደሬዳዋ ከተሞች በወንዶች ፉክክር የተጀመረ ሲሆን ነገ ፍፃሜ እንደሚያገኝ ይጠበቃል፡፡ በቅርጫት\nኳስ ስፖርት ትልቅ አቅም ያላቸው እንደ አዲስ አበባ ያሉ ከተሞች ተሳታፊ ባልሆኑበት ውድድር የተፎካካሪዎች ቁጥር በዘንድሮው ዓመት\nማሽቆልቆሉ የፉክክሩን ድባብ ቢያቀዛቅዘውም ራቅ ካለ ከተማ የመጡ ተሳታፊዎች ውድድሩን አድምቀውታል፡፡ በወንዶች መካከል በሚደረገው\nፉክክር አዘጋጁ ቢሾፍቱ ከተማን ጨምሮ አዳማ፣ድሬዳዋ፣ሐረሪ፣ቡታጅራ ከተሞች እንዲሁም የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ተሳታፊ\nሆነውበታል፡፡ በሴቶች መካከል በሚደረገው ፉክክር ግን ባልተጠበቀ መልኩ አሰላ ከተማና የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ብቻ ተሳታፊ\nሆነዋል፡፡ ከመሐል\nአገር ራቅ ያሉ ከተሞች በውድድሩ ለመሳተፍ ያሳዩትን ተነሳሽነት ያህል በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኙ ከተሞች በፉክክሩ ላይ መገኘት\nአለመቻላቸው ከበጀት እጥረት ጋር ተያይዞ መሆኑ አብዛኞቹን የአገራችን ከተሞች ለስፖርቱ እየሰጡት ያለውን ትኩረት ትዝብት ላይ የጣለ\nነው፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ ከተሞች በውድድሩ መሳተፍ ያልቻሉት የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን በሚያዘጋጀው የቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር\nሊግ ላይ ተሳታፊ በመሆናቸው ምክኒያት እንደሆነ የፌዴሬሽኑ የስራ ሂደት ዳይሬክተር አቶ ይመር ሃይሌ ለአዲስ ዘመን ገልፀዋል፡፡\nውድድሩ ከተጀመረ ቀን አንስቶ በሁለቱም ፆታ የዙር ፉክክሮች እየተስተናገዱ\nይገኛል፡፡ ዛሬ በወንዶች ድሬዳዋ ከተማ ከአዳማ ከተማ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ የሚጠበቅ ሲሆን ቡታጅራ ከተማ ከሐረሪ ከተማ ጋር\nየሚያደርጉት ፉክክርም ይከናወናል፡፡ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚና ቢሾፍቱ ከተማም የሚገናኙ ይሆናል፡፡ ነገ ውድድሩ ሲጠናቀቅ\nደግሞ በሴቶች አሰላ ከተማ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ በዙር ውድድር የሚገናኙ ሲሆን በዚህ ጨዋታ አጠቃላይ አሸናፊው የሚለይም\nይሆናል፡፡ በተመሳሳይ ድሬዳዋ ከተማ ከሐረሪ ከተማ፣ አዳማ ከተማ ከቢሾፍቱ ከተማ፣ ቡታጅራ ከተማ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ\nጋር በወንዶች የሚያደርጉትን ጨዋታ ተከትሎ የ2012 ዓ.ም የከተሞች የቅርጫት ኳስ ቻምፒዮን የሚለይ ይሆናል፡፡አዲስ ዘመን ጥር 28/2012ቦጋለ አበበ ", "passage_id": "1c5e243289e75d40e615dcb29a33eb04" }, { "passage": "የዓለምአቀፉ የእግርኳስ አስተዳዳሪ አካል በአዲስ አበባ የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ ለመክፈት እንቅስቃሴዎች ከጀመረ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡ የፊፋው ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ለካፍ ጠቅላላ ጉባኤ ኢትዮጵያ በ2009 በተገኙበት ወቅት ለቢሮው መከፈት አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ለማሟላት ቃል መግባታቸውን ተከትሎ ነው ይህ ቢሮው አዲስ አበባ ላይ የሚከፈተው፡፡ፊፋ ነገ ጠዋት ተወካዩን ወደ አዲስ አበባ የሚልክ ሲሆን ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌድሬሽን ሃላፊዎች ጋር አርብ ውይይት በቢሮው ጉዳይ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ የፊፋ ተወካዩ በአዲስ አበባ በሚኖረው ቆይታ ለቢሮ የሚሆኑ ህንፃዎችን እንደሚመለከት እና ለቢሮ የሚሆኑ ቦታዎችን እንደሚመርጥ ታውቋል፡፡ ቅዳሜ ወደ ስዊዘርላንድ ሲመለስም ለፊፋ የበላይ ሃላፊዎች ሪፖርት በማቅረብ ቢሮው የሚከፈትበትን ግዜ እንደሚያጤን ይጠበቃል፡፡ክፍለ አህጉራዊው ቢሮ የምስራቅ አፍሪካ ሃገራትን እንዲያገለግል የሚከፈት ሲሆን ሃገራት የሚያስፈልጋቸው እርዳታ እና ከፊፋ ጋር ያላቸው ግንኙነት ለማጠንከር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል፡፡ ፊፋ እንዲህ ዓይነት ቢሮ በአፍሪካ ሲከፍት ይህ ለሶስተኛ ግዜ ነው የሚሆነው፡፡ ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ቢሮዎች በደቡብ አፍሪካ እና ሴኔጋል ይገኛሉ፡፡", "passage_id": "7ca147a153c729d898e552dc75f4f34e" }, { "passage": "የዳን ፈተናው በአማራ ክልል ከ11 ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ለተውጣጡ ከአንደኛ እስከ አራተኛ ‹ዳን› ላላቸው 190 የወርልድ ቴኳንዶ ስፖርተኞች ነው እየተሰጠ የሚገኘው።የአማራ ክልል ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ባለሙያ አቶ አቤል ይልቃል እንደተናገሩት ፈተናው በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የወርልድ ቴኳንዶ ስፖርተኞችን የዳን ደረጃ ለማሻሻልና ስፖርቱን ለማሳደግ ያለመ ነው። ከዚህም ጎን ለጎን ክልሉን ወክለው በሀገር አቀፍ ፣ በሀጉር አቀፍና በዓለም አቀፍ ወርልድ ቴኳንዶ ውድድሮች የተሻለ ውጤት ሊያመጡ የሚችሉ ስፖርተኞችን ለማፍራት የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል።", "passage_id": "fab15c208231677cbf0a0d38ad93c18a" }, { "passage": "ባየር ሙኒክ በኢትዮጵያ በሚከፍተው የታዳጊዎች የስፖርት ማዕከል ዙርያ ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጋር የትብብር ሰነድ ሲፈራረም በዕለቱ በታዳጊዎች መካከል በተደረገው ውድድር ኢትዮጵያ መድን የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል።በኢትዮጵያ የእግርኳስ አካዳሚ ለመክፈት ቅድመ ስምምነቶችን ለመፈፀም ከእሁድ ጀምሮ አዲስ አበባ የገቡት የባየር ሙኒክ የልዑካን ቡድን ዛሬ ረፋድ ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የስምምነት ፊርማ ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጋር አድርጓል። የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ርስቱ ይርዳው፣ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንት አቶ ኢሳያስ ጂራ እና የባየር ሙኒክ ተወካዮችም በዚህ ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተዋል።ለሦስት ዓመታት በሚቆየው በዚህ ሰምምነት መሠረት የባየር ሙኒክ በኢትዮጵያ የ17 ዓመት በታች ታዳጊዎች ማሰልጠኛ አካዳሚ የሚከፍት ይሆናል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ እግርኳስን ለማሳደግ የቴክኒክ እና የአስተዳደር ሥልጠናዎችን ባለሙያዎችን በመላክ እንደሚያወናውን የተነገረ ሲሆን የተወሰኑ በሀገር ውስጥ የሚሸፈኑ ወጪዎች ካልሆነ በቀር የአካዳሚውን ሙሉ ወጪ የጀርመነ ክለብ የሚሸፍን ይሆናል። ይሁን እንጂ አካዳሚው መቼ እና የት ይከፈታል የሚለውን ከወዲሁ መግለፅ አልተቻለም።ከስምምነቱ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ ከብራዚላዊው የቀድሞ የባየር ሙኒክ አጥቂ ጂኦቫኒ ኤልበር ጋር በብሔራዊ ቡድን እና ተዛማች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በተናጥል ውይይት አድርገዋል።በታዳጊዎች በኩል ምን እየተሰራ መሆኑን ለማሳየት በማሰብ በአአ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር በሚካሄደው ከ17 ዓመት በታች ውድድር ላይ ከሚካፈሉ ቡድኖች መካከል ስምንት ክለቦች በሁለት ምድብ ተከፍለው ባካሄዱት ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ኢትዮጵያ መድን ለፍፃሜ ዋንጫ ደርሰው ኢትዮጵያ መድን 2-0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዕለቱን ዋንጫ ከጂኦቫኒ ኤልበር እጅ ተቀብለዋል።", "passage_id": "b00e81d13e1fcc13e82dd89d829d3e43" } ]
a6923c06c4f8296153dd4b3318c05c94
a13d4682ea6c8101e24c752970fd973f
ለጥቁር ሕዝቦች የታገሉ የስፖርቱ ዓለም ከዋክብት
የተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከአስር ዓመት በፊት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመለክተው በተለያዩ ዓለምአቀፍ የስፖርት መድረኮች ስፖርተኞች በዘርና በቆዳ ቀለማቸው መገለል የተለመደ እንደሆነ ያትታል። ይህ እውነታ አሁን ላይ አደጉ በምንላቸው አገራት ስፖርት ላይ እንኳን ነቀርሳ መሆኑን በተለያዩ አጋጣሚዎች እንመለከታለን። በተለይም እንደ አሜሪካ፤ አውስትራሊያና አውሮፓ የመሳሰሉ አገራት ላይ ጥቁር ስፖርተኞች አሁንም ድረስ በዘረኝነት ሲዘለፉ፤ ሲንቋሸሹና ዝቅ ተደርገው የሚታዩባቸው አጋጣሚዎች እየተበራከቱ መምጣታቸው ከዘር፤ ከሃይማኖትና ከፖለቲካ ነፃ መሆን የሚገባው ስፖርት ላይ መጥፎ አሻራ እንዲያርፍ እያደረገ ይገኛል። በስፖርት ጥቁሮች አሁን ላይ በየትኛውም ዓለምአቀፍ መድረክ ተፎካካሪ እንዲሆኑ ከማስቻል ባሻገር በትልቅ ደረጃ ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ለማሳየት በርካታ ጥቁር ከዋክብት ብዙ ችግሮችን ተጋፍጠዋል። በተለይም ጥቁር አሜሪካውያን አትሌቶች በዚህ ረገድ ያዩት ፈተና ሳይጠቀስ የሚታለፍ አይደለም። አፍሪካውያንም ቢሆኑ በርካታ መከራዎችን ተጋፍጠው ለታላቅ ክብር በመብቃት ለአሁኖቹ አትሌቶች ፋና ወጊ ሆነው እኩልነትን ማንፀባረቃቸው አይካድም። ለዚህም ታሪካዊውን ኢትዮጵያዊ የማራቶን ኮከብ አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ በትልቁ የሚነሳ የጥቁር ህዝቦች ኩራት ሆኖ እናገኘዋለን። ኢትዮጵያውያን በስፖርቱ ብቻም ሳይሆን በዓደዋ ድል የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌትና የመዓዘን ድንጋይ ሆነዋል። የጥቁር ህዝቦች ኩራት የሆነው የዓደዋ ድል የሚዘከርበት የካቲት ወር በመላው ዓለምም የጥቁር ህዝቦች መታሰቢያ ሆኖ ይከበራል። በስፖርቱ ዓለም ለእኩልነት የታገሉ ቁንጮ አትሌቶችም በዚህ ወር ሳይዘከሩ አይታለፉም። በእርግጥ በስፖርት መድረክ ዘረኝነትን የታገሉ፤ እኩልነትን ያንፀባረቁና በድላቸው የጥቁር ህዝቦችን አንገት ያቀኑ በርካታ ጥቁር ከዋክብቶች መኖራቸው አይካድም። ከእነዚህ ከዋክብቶች ግን ተፅዕኗቸው ከፍተኛ የነበረ፤ ድላቸው በርካታ ትርጉም የነበረውና በትልቅ ደረጃ የሚነሱትን ሦስት ጀግኖች ብቻ በዓድዋ ድል ዋዜማ ላይ ሆነን በስፖርት ማህደር አምዳችን እንመልከት። አበበ ቢቂላ 1928 ፋሺስት ጣሊያን በአምባገነኑ ቤኒቶ ሞሶሎኒ ኢትዮጵያን ወረረ፤ ምስጋና ለማይዘነጉት ጀግኖቹ አርበኞቻችን ይግባና ሞሶሎኒና ግብረአበሮቹ ብዙም ሳይደላደሉ ከአገር ቤት በቅሌት ተባረሩ። ከሃያ አራት ዓመታት በኋላ ታላቁ አበበ ቢቂላ ሮምን በባዶ እግሩ ወሮ ዓለምን ጉድ አሰኘ፤ የምን ጊዜም የማራቶን ንጉሡ የአፍሪካውያን ኩራትና የነፃነት ተምሳሌት እንዲሁም፤ የመጀመሪያው ጥቁር የማራቶን ኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ በጥቁሮቹ በጀግኖቹ መታሰቢያ ወር የካቲት የጥቁር ህዝቦች ኩራት ሆኖ ከሃምሳ አምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመት ዋዜማ በሮም ኦሊምፒክ የፈፀመው ታሪካዊ ጀብድ በመላው ዓለም ያሉ ጥቁር አትሌቶችን በእጅጉ ያኮራና ያነሳሳ ነበር። ጷግሜ 5ቀን 1952 አስራ ሰባተኛው የሮም ኦሊምፒያድ በታላቋ ሮም ጎዳናዎች አንድ ተዓምር ታየ፤ በርካቶች ዓይናቸውን ለማመን ተቸገሩ፤ በአንባገነኑ ሞሶሎኒ አገር በበርካታ ነጮች መሃል አንድ ጥቁር በባዶ እግሩ ታየ። የጥቁር ህዝቦች ተዓምርን ለመቀበል የሚተናነቃቸው ዘረኝነትን በደማቸው ያሰረፁ ነጮች እንዴት ይህ ሊሆን እንደቻለ ግራ ተጋቡ። አፍሪካውያንን ያኮራ ኢትዮጵያውያንን ከልብ ያስፈነጠዘ ታሪካዊ ድል። የአራት ዓመት ታዳጊ ሆኖ እናት አገሩ ኢትዮጵያ በጣሊያን ፋሺስት ስትወረር መጥፎውን ጊዜ ገና ባልጎለበተ የሕፃን አዕምሮው የሚያስታውሰው አበበ ቢቂላ ሃያ ስድስት ዓመታት ጠብቆ ታላቁን የሮም ጎዳና በባዶ እግሩ ወሮ የማይደገመውን ታሪክ ሠራ። ከአራት ዓመት በኋላም 1956 በድጋሜ ጫማ አጥልቆ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፎ ጥቁሮች በማይደፈረው ርቀት አሁን ላይ ቁንጮ እንዲሆኑ መሰረቱን አኖረ። እሱ በከፈተው በርም ቁጥር ስፍር የሌላቸው የማራቶን አትሌቶች ለዘመናት ርቀቱን የግላቸው አድርገው አሁን ድረስ ዘልቀዋል። ጄሴ ኦውንስ ታላቁ የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ እንደ 1936ቱ በዘረኝነት የተጨማለቀበትን ወቅት ማስታወስ ከባድ ነው። ገና ከጅምሩ አይሁዶችንና ጥቁሮችን ከኦሊምፒኩ ለማግለል እንዲሁም የነጮችን የበላይነት አስተሳሰብ የመደገፍ አባዜ የተጠናወተው ዘረኛው የናዚ መሪ አዶልፍ ሂትለር ውድድሩ በአገሩ ጀርመን እንደሚካሄድ ካወቀ አንስቶ ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም። ይህ ኦሊምፒክ ብዙ ተቃውሞ ቢገጥመውም ከውድድሩ ራሳቸውን ያገለሉና እንዳይሳተፉ የተደረጉ አይሁዳውያን ነበሩ። በውድድሩ የተሳተፉትም ቢሆኑ በሂትለር ትዕዛዝ የተገለለ የመለማመጃ ሜዳና የውድድር ቁሳቁስ እንዲጠቀሙ ተደርገዋል። ጥቁሮችም በዚህ ኦሊምፒክ ተመሳሳይ ዕጣ ፋንታ የገጠማቸው ሲሆን የበታች እንደሆኑ ለማሳየት ያልተደረገ ጥረት አልነበረም። ይህን ጥረት ሁሉ ውድቅ አድርጎ የሂትለርን ቆሽት ያሳረረ አንድ ክስተት ግን በጥቁሩ አሜሪካዊ አትሌት ጄሴ ኦውንስ ተፈፀመ። ኦውንስ በዚህ የበርሊን ኦሊምፒክ በመቶ፤ በሁለት መቶ፤ በረጅም ዝላይና አራት በመቶ የዱላ ቅብብል ውድድሮች አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ጠራርጎ በመውሰድ ጥቁሮች አንገታቸውን ያቀኑበት ነጮች ደግሞ የተሸማቀቁበትና ለመቀበል ያቃራቸውን ድል አጣጣመ። ይህ አልዋጥለት ያለው ሂትለር ግን በሽልማት ስነ ስርዓቱ ላይ ኦውንስን ላለመጨበጥና ለድሉም እውቅና ላለመሰጠት ራሱን አሳምኖ ስቴድየሙን በድንፋታ ለቆ ወጣ። የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ፍራንክሊን ሩዝቬልትም ቢሆኑ ለኦውንስ ድል እውቅና ሳይሰጡት ቀርተዋል። ኦውንስ ይህ ገድሉ በዘረኛ ነጮች እውቅና ይነፈገው እንጂ ነጮች ወደዱም ጠሉም ከጥቁሮች እኩል እንደሆኑ ልቦናቸው እንዲያምን አስገድዷቸዋል። በአንድ አገር ውድድሮች የነጭና የጥቁር ተብሎ ተከፍሎ በሚካሄድባት አሜሪካም በወቅቱ የኦውንስ ድል ትልቅ ትርጉም ነበረው። በዚህም ኋላ ላይ እኤአ 1976 የአሜሪካውያን ትልቁ ሽልማት የሆነውን የነፃነት ሜዳሊያ ሊሸለም በቅቷል። ኦውንስ ህይወቱን በሙሉም የጥቁሮች መብት እንዲከበር ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ጥብቅና ከመቆም ባሻገር የእሱን ፋና ተክለው ለመጡ ጥቁር አትሌቶች ሁሉ ትልቅ የመንፈስ ብርታት በመሆን ከጎናቸው ሲቆምና ሲሟገት ኖሯል። መሐመድ አሊየምን ጊዜም የቦክስ ስፖርት ንጉሡ መሐመድ አሊ የዓለም የቦክስ ቻምፒዮንና ታላቅ የቡጢ ተፋላሚ ብቻ አልነበረም። የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፤ የጥቁር ህዝቦች ሰንደቅ፤ በመላው ዓለም በስፖርትና በታላቅ ስብዕና ተምሳሌትም ጭምር ነው። ብዙዎች ቦክስ ስፖርት ሳይሆን የጥጋበኞች ድብድብ አድርገው ከመሳል አስተሳሰብ አውጥቶ የቦክስን ስፖርት ጥበባዊ ገፅታ በማላበስ ተወዳጅና አሁን ላይ በዓለማችን በአንድ ጊዜ በርካታ ሚሊየን ዶላሮች የሚያሳቅፍ ግንባር ቀደም ስፖርት እንዲሆን ተፅዕኖውን አሳርፏል። መሐመድ የትውልድ ስሙ ካሴስ ክሌይ ቢሆንም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ባሮችን ነፃ ለማውጣት በታገሉ ታላቅ ሰው መታሰቢያነት የወጣለት ስም ነበር፡፡ ለመጀመርያ ጊዜ የዓለም ከባድ ሚዛን ቻምፒዮን ከሆነ በኋላ በማግስቱ ስሙን ለመቀየር ወሰነ፡፡ የነፃነት ታጋዩን ማልኮለም ኤክስ ከጎኑ አድርጎ በሰጠው መግለጫ «ዘ ኔሽን ኦፍ ኢስላም» የተባለውን ተቋም መቀላቀሉን በማሳወቅ የባርያ ስም ይለው የነበረውን ካሴስ ክሌይ በመቀየር በቀድሞ ስሙ ላለመጠራት ወሰነ። በወቅቱ «ኔሽን ኦፍ ኢስላምን» ይመራ የነበረው ኤልጅያህ መሃመድ እኤአ በ1964 ላይ መሐመድ አሊ የሚለውን ስም ካወጣለት በኋላ እሱን በማፅደቅ እስከ ህይወት ዘመኑ መጨረሻ ተጠራበት። ታሪካዊው ኢትዮጵያዊ አትሌት አበበ ቢቂላ በ196o የሮም ኦሊምፒክ በባዶ እግሩ ሮጦ ለጥቁር ህዝቦች የመጀመሪያውን የማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ሲያስመዘግብ መሐመድ አሊም በቦክስ የወርቅ ሜዳሊያ አጥልቆ ነበር። ሁለቱ ታሪካዊ የጥቁር ህዝቦች ከዋክብት ፊርማቸውን ተለዋውጠውም ነበር። ይሁንና መሐመድ አሊ ይህን የወርቅ ሜዳሊያውን ለአገሩ ከማበርከት ይልቅ በሊውስ ቪል ግዛት በሚገኘው የኦሃዮ ወንዝ ጨምሮታል። ሜዳሊያውን ለአሜሪካና ለትውልድ ከተማው ሊውስ ቪል ቢቀዳጅም በርገር የመግዛት መብት ባለመኖሩ ተቃውሞውን ለመግለፅ ነበር ይህን ርምጃ የወሰደው። በ1996 አገሩ አሜሪካ ባስተናገደችው የአትላንታ ኦሊምፒክ ችቦውን እንዲለኩስ ከመደረጉ ባሻገር ወንዝ የጨመረው የወርቅ ሜዳሊያ ምትክ ሌላ ሜዳሊያ በአንገቱ ተጠልቆለታል። በ1970 የዶክተር ማርቲን ሉተር ኪንግ መታሰቢያ ሽልማት የተቀበለው መሐመድ አሊ፤ የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነት ተምሳሌት ሆኖም ያውቃል። የተባበሩት መንግሥታት የሰላም መልዕክተኛ ሆኖም ከ1998 እሰከ 2008 በታዳጊ አገራት በመዘዋወር አገልግሏል። ታላቁን የደቡብ አፍሪካ ነፃነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ከእስር እንደተፈቱ በአካል ተገኝቶ ደስታውን ለመግለፅ መሐመድን የቀደመው አልነበረም። አዲስ ዘመን የካቲት 22/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28169
[ { "passage": " በስፖርቱ ዓለም ጥሩ የአካል ብቃት፣ሰውነትን እንደ ልብ የማዘዝ ችሎታ፣ፅናት፣ጥንካሬና ፍጥነትን ከሚሹ ጨዋታዎች መካከል ባድሚንተን ዋነኛው ነው። ከሜዳ ቴኒስ ወይንም ከጠረጴዛ ቴኒስ ጋር ተመሳሳይ አጨዋወትን የሚጋራው የባድሚንተን ስፖርት በብሪታኒያና ህንድ እንደጎለበተ የሚነገር ቢሆንም በአውሮፓዊቷ አገር ዴንማርክ ትልቅ ዝና አለው። ይህ ስፖርት ተወዳጅነቱን እያሰፋ በኤሽያ አገራት በስፋት መዘውተሩን ተከትሎም ባለፉት ጥቂት የማይባሉ ዓመታት የቻይና የበላይነት የሚንፀባረቅበት ሆኗል። እኤአ 1992 በባርሴሎና የበጋ ወራት ኦሊምፒክ ተካቶም በአራት የውድድር ዘርፎች አገራት ተፎካካሪ ሆነውበታል። በነጠላ ወንዶች፣ ነጠላ ሴቶች፣ በቡድን ሴቶችና በቡድን ወንዶች ኦሊምፒክ ላይ የነበረው ፉክክር አድጎም በድብልቅ ፆታ አምስተኛ የመወዳደሪያ ዘርፍ ለመሆን ጊዜ አልፈጀበትም። የባድሚንተን ስፖርት በኢትዮጵያ በይፋ መቼ እንደተጀመረ ሰነዶችን ማግኘት አይቻልም። ይሁን እንጂ ይህ ስፖርት በ1940ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በታወቁ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች፣ የሚሲዮን ተቋማትና በወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማህበር (ወክማ) አካባቢ በውጭ አገር ዜጎችና መምህራን አማካኝነት እንቅስቃሴው እንደተጀመረ ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በተለይም የባድሚ ንተን ስፖርት በ1970 ዎቹ ገደማ ከወክማ ባሻገር በህንድ ኤምባሲ ውስጥ በስፋት መዘውተር እንደ ጀመረ ይነገራል። በህዳር ወር 1978 ዓ.ም ስፖርቱ በአደራጅ ኮሚቴነት ተዋቅሮ በሂደት 1982 ዓ.ም ላይ አደረጃጀቱ ወደ ፌዴሬሽን አድጓል። ከዚህም በኋላ ከ1986 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የኢትዮጵያ ቻምፒዮናን በውድድር ደረጃ ማከናወን ችሏል። ባለፉት ዓመታትም በአገራችን በሚካሄዱ እንደ መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች፣የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል፣የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድሮችና ሌሎችም ፉክክሮች ላይ የምንመለከተው ስፖርት መሆን ችሏል። ከኦሊምፒክ ስፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው የባድሚንተን ስፖርት በተለይም በኤሽያ አገራት በስፋት የሚዘወተር ብቻ ሳይሆን እነዚህ አገራት በብዛት ኦሊምፒክ ላይ ተሳትፈው በሜዳሊያ ሰንጠረዥ የአገራት ፉክክር ውስጥ የሚገቡበት የስፖርት አይነት ነው። የባድሚንተን ስፖርት አሁን ላይ በአገራችን ብዙ እውቅና ከሌላቸው የስፖርት አይነቶች አንዱ ሆኖ እናገኘዋለን። የአገራችን መገናኛ ብዙሃንም አብዛኞቹ ለዚህ ስፖርት ትኩረት ሲሰጡት አይታይም። ስፖርቱን በቅርበት ከሚያውቁት ባሻገ ርም አብዛኛው ህዝብ ባድሚንተን ምን እንደሆነ ግን ዛቤ አለው ለማለት ይቸግራል። በአጠቃላይ የባድሚንተን ስፖርት በአገራችን ካለመስፋፋቱ ባሻገር ሌሎች የኦሊምፒክ ስፖርቶች በሚጓዙበት የእድገት ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው ለማለት አይቻልም። ለመሆኑ ይህ ስፖርት እንደ እግር ኳስና አትሌቲክስ ባይሆን እንኳን ሌሎች ደካማ የሚባሉት ስፖርቶች በሚንቀሳቀሱበት ደረጃ ለመንቀሳቀስ ለምን ተሳነው?፣ ክለቦችን መስርተው የሊግ ውድድሮችን በቀጣይነት ለማስኬድ ዳዴ ከሚሉት አንዳንድ ፌዴሬሽኖችስ በምን ይለያል? የሚሉ ጥያቄዎች በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ ይነሳሉ። የስፖርቱ አፍቃሪዎች ከስፖርቱ ባህሪ ተነስተው ለነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ የባድሚንተን ትልቁ ችግር መሰረተ ልማት እንደሆነ ያብራራሉ። የባድሚንተን ስፖርት በባህሪው ከቤት ውስጥ ስፖርቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የተሟላ መሰረተ ልማት የሚጠይቅ ነው። ስለዚህ ስፖርቱን ለማስፋፋትና ለማዘውተር ቢያንስ መሰረታዊ የሆነ አዳራሽ ወይም ጅምናዚየም ያስፈልጋል። የባድሚንተን መጫወቻዋ ላባ(በተለምዶ እፉየ ገላ\nየምትመስል መጫወቻ) በጨዋታ\nወቅት በንፋስ ምክንያት\nአቅጣጫ የመለዋወጥ ባህሪ\nስላላት ስፖርቱን ከቤት\nውጭ ማድረግ አስቸጋሪ\nነው። ይህን ስፖርት\nለመጫወት አዳራሹ ወይንም\nጅምናዚየሙ ቢያንስ ሰባት\nሜትር ከፍታ ያለውና\nሁለት ጨዋታዎችን በአንድ\nጊዜ ማካሄድ የሚያስችል\nመሆን እንዳለበት ዓለም\nአቀፍ ህጉ ይደነግጋል።\nበአገራችን አብዛኞቹ ስፖርቶች\nከቤት ውጭ ሊዘወተሩ\nይችላሉ። ባድሚንተን ግን\nቤት ውስጥ ብቻ\nየሚደረግ ውድድር በመሆኑ\nበቀላሉ እንዳይዘወተርና እንዳይስፋፋ\nእንቅፋት መሆኑን የስፖርቱ\nቅርብ ሰዎች ይናገራሉ።\nከአዲስ አበባና ድሬዳዋ\nከተሞች በስተቀር ስፖርቱን\nሌሎች ክልሎች ላይ\nእንደልብ ማካሄድና ማስፋፋት\nየሚያስችል መሰረተ ልማት\nየለም። በአዲስ አበባ\nወክማ ውስጥ ባድሚንተን\nበስፋት እንደሚዘወተር ይታወቃል።\nነፃ የሆኑ አዳራሾች\nወይም ጅምናዚየሞች ቢኖሩ\nስፖርቱ የሚፈልጋቸው ሌሎች\nቁሶችን በቀላሉ ማግኘት\nእንደሚቻል ይታመናል። በእርግጥ\nየባድሚንተን ስፖርትን እንደ\nቮሊቦልና ቅርጫት ኳስ\nአይነት ስፖርቶች ከቤት\nውጪ ማዘውተር የሚቻልበት\nእድል ዝግ አይደለም።\nይሁን እንጂ ባድሚንተንን\nከቤት ውጭ ማዘውተር\nስፖርቱን በፕሮፌሽናል ደረጃ\nለማሳደግና ውጤታማ ለመሆን\nእንደማይቻል እውን ነው።\nአገር አቀፍ ፌዴሬሽኑ\nስልጠናዎችን ለመስጠት አይደለም\nአገር አቀፍ ውድድሮችን\nለማካሄድ እንቅፋት ከሆኑበት\nነገሮች ዋነኛውም ይሄው\nማዘውተሪያ ስፍራው መሆኑም\nይታመናል። ስፖርቱ እጅግ የሚወደድና የብዙዎችን ቀልብ ሊስብ የሚችል ነው። በአገራችን በተለያዩ ውድድሮች ላይ እንደሚታየውም ወጣቱ ስፖርቱ ላይ ትልቅ ፍላጎት አለው። በተለይም በለጋ እድሜ ላይ የሚገኙ እድሜያቸው አሥራ አንድና አሥራ ሁለት አካባቢ የሚገኙ ታዳጊዎች ለባድሚንተን ስፖርት ከፍተኛ ፍላጎት አላቸው። ሁኔታዎች ተመቻችተው እንደ ስፖርት ለሁሉም እድሜያቸው የገፋ ሰዎች ቢያዘወትሩትም ይመከራል። የባድሚንተን ስፖርት በደንብ ትኩረት ተሰጥቶት ተከታታይ ስልጠናና በርካታ ውድድሮች ቢደረጉ ቢያንስ በአፍሪካ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ይታመናል። አሁን ባለው ሁኔታ ስፖርቱ ከነችግሮቹ እንኳን ውጤቱ ብዙ ባይሆንም በመላ አፍሪካና ሌሎች ዓለም አቀፉ ጨዋታዎች መሳተፍ እየተቻለ ይገኛል። መንግሥት ስፖርቱን በተመለከተ ሥራው በዋናነት ስፖርቱን ማስፋፋት ነው። የልማት ሥራዎችን መስራት ደግሞ ያለበት ፌዴሬሽኑ ነው። ፌዴሬሽኑን ሊመሩ የሚችሉ ደግሞ ሥራ አስፈፃሚዎች ተቀምጠዋል። እነዚህ ሥራ አስፈፃሚዎች ሃብት አሰባስበው ስፖርቱን በደንብ በማህበረሰቡ ውስጥ እንዲያስፋፉ ትልቅ ድርሻ ያላቸው ህዝባዊ አካል ናቸው። መንግሥት እንደማንኛውም የስፖርት ፌዴሬሽን ለባድሚንተንም ድጋፍ ያደርጋል። እንዲያውም መንግሥት አሁን የሚያደርገው ድጋፍ ከስፖርቱ እንቅስቃሴ አንፃር ጥሩ የሚባል እንደሆነ ማስቀመጥ ይቻላል። ባድሚንተን የኦሊምፒክ ስፖርት እንደመሆኑ እንደሌሎች መሰል ስፖርቶች በታዳጊ ወጣቶች የተለያዩ ፕሮጀክቶችና በአካዳሚ ደረጃ ሰፊ እንቅ ስቃሴ ሲደረግበት አይታይም። ባድሚንተን በሁሉም ክልሎች በታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት ከሚሰራባቸው ስፖርቶች አንዱ ሆኖ እየተሰራ ይገ ኛል። ፌዴሬሽኑም በየዓመቱ የሚደረጉ የፕሮጀክቶች የምዘና ውድድሮችም ተሳታፊ ነው። በታዳጊ ፕሮጀክት ደረጃ የሚሰራባቸው በአካዳሚ ደረጃ ግን ስልጠና የማይሰጥባቸው ሌሎች ስፖርቶችም አሉ። በባድሚንተን ስፖርት በግለሰቦች የሚመሰረቱ ቡድኖች አሉ፣ እንደ ክለብ ግን ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ አይደሉም። በዚህ ሁኔታ በባድሚንተን ስፖርት በተለያዩ ክልሎች የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀ ክቶችን ቀርፆ መንቀሳቀስ እንደ አገር ስፖርቱን ከመጥፋት ሊታደግ ይችላል። ይሁን እንጂ ከነዚህ ፕሮጀክቶች የሚወጡ ታዳጊዎች ወደ አካዳሚ ገብተው ከዚያም ወደ ክለብ መሸጋገር ካልቻሉ ከስፖርቱ ጋር ያላቸው እህል ውሃ የሚዘልቀው እስከ ምዘና ውድድር ድረስ ነው። ይህ ደግሞ ብዙ ወጣቶች\nወደ ስፖርቱ እንዳይመጡ\nእንቅፋት መሆኑ አይቀርም።\nክለቦች ከሌሉ ከፕሮጀክት\nየሚወጡ ታዳጊዎች ተጎጂ\nሊሆኑ እንደሚችሉ ቢታመንም\nከፕሮጀክት ከወጡ በኋላ\nሌላ ማረፊያ የላቸውም።\nበአገር አቀፍ ደረጃ\nበሚካሄዱ ውድድሮች ክልላቸውን\nወክለው መሳተፍ አንዱ\nአማራጫቸው መሆኑ ግን\nይታመናል። ከባድሚንተን ጋር በተመሳሳይ በጀት ይንቀሳቀሱ የነበሩ በርካታ ፌዴሬሽኖች ክለቦችን በማቋቋምና ውድድሮችን በብዛት በማድረግ ራሳቸውን እያሳደጉ እንደሚገኙ ብዙ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። በአገራችን ከታሪካቸውም አንፃር የኳስ ስፖርቶች ላይ ትኩረት የማድረግ ልምድ ስላለ የኳስ ስፖርቶችና ባድሚንተን እኩል ማየት ተገቢ አይደለም። የኳስ ስፖርቶች የሚባሉት እግር ኳስ፣እጅ ኳስ፣ቅርጫት ኳስ ወዘተ በሚሊተሪ አካባቢ ሰፊ መሰረት ስላላቸው እነሱን ለማሳደግ ከባድሚንተን አይነት ስፖርቶች አኳያ ብዙ ልፋት እንደማይጠይቅ የሚሞግቱ የስፖርት ቤተሰቦች ጥቂት አይደሉም። የባድሚንተን ስፖርት በርካታ ችግሮች ቢኖ ሩበትም በአንዳንድ ክልሎች መሰረታዊ ነገር ሳይሟ ላላቸው ጭምር እየሰሩ ነው። ስፖርቱ የመሰረተ ልማት እጥረት ቢኖርበትም ፌዴሬሽኑ በተቻለው አቅም ከዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኑ ከሚያገኛቸው የቁሳቁስ ድጋፍ ተነስቶ ለክልሎች ድጋፍ እየሰጠ ነው። ይህ ስፖርቱ እንዲያንሰራራ ትልቅ እድል ነው። የመሰረተ ልማት ጉዳይ የባድሚንተን ስፖርት ብቻም ሳይሆን የበርካታ ስፖርቶች እንቅፋት እንደመሆኑና ከአገር አቅም ጋር የተያያዘ መሆኑ ችግሮች በአንድ ጀምበር ሊፈቱ አይችሉም። ያም ሆኖ ኢትዮጵያ በስፖርቱ መሰረተ ልማት ግንባታ ረገድ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ለመሆኗ በተለያዩ ክልሎች ግዙፍ ስቴድየሞችን ጨምሮ ጅምናዚየምና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ማስተዋል ይቻላል። ባድሚንተንን ለመሳሰሉትና በመሰረተ ልማት ችግር በአገራችን መራመድ ያልቻሉት ስፖርቶችም የነዚህን መሰረተ ልማት ግንባታዎች መጠናቀቅ በተስፋ የሚጠበቁ ይሆናል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 27/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "4c64656042e6ddb504d280c730f6b584" }, { "passage": "በሩሲያ አስተናጋጅነት በቀጠለው የዓለም ዋንጫ አሁንም አፍሪካን የወከሉት ቡድኖች ድል ርቋቸዋል። ዛሬ ከፖላንድ ጋር በምታደርገው ጨዋታ ጉዞዋን የምትጀምረው ሴኔጋልን የዓለም ዋንጫ ጉዞ ተስፋ እና ስጋት እንዲህ አቅርበናል።ሴኔጋል ከ16 ዓመት ቆይታ በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫው ተመልሳለች። በካንሰር ህመም ምክንያት አሁን በህይወት በሌሉት ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ብሩኖ ሜትሶ እየተመሩ የቴራንጋ አናብስቱ በመጀመሪያ ተሳትፏቸው እስከሩብ ፍፃሜ የዘለቀ ድንቅ ጉዞን አድርገዋል። ያን ግዜ የብሄራዊ ቡድኑ አምበል የነበረው አሊዩ ሲሴ አሁን ደግሞ በአሰልጣኝነት ቡድኑን እየመራ ወደ ዓለም ዋንጫው መልሷል።ተስፋሴኔጋል በልምድ እና ተስጥኦ የታጨቀ የቡድን ስብስብ ባለቤት ነች። በፊት መስመር ላይ ያሉት ተጨዋቾች ያላቸው ፍጥነት እና ክህሎት ቡድኑ ረጅም ጉዞ እንዲጓዝ ሊያግዘው ይችላል። ሙሳ ሶው፣ ኬታ ባልዴ እና ሳዲዮ ማኔን ያካተተው ይህ ስብስብ ለየትኛውም ቡድን ፈተና እንደሚሆን የታወቀ ነው። በተለየ በእንግሊዝ መልካም ግዜያትን ያሳለፈው ማኔ ይህንን ብቃቱን በዓለም ዋንጫው መድገም ከቻለ ለሴኔጋል ጥሩ ነው። ኮያቴ እና ጋይ ለተከላካዮች ሽፋን በመስጠት የአማካይ ክፍሉን ማጠናከራቸው ለሴኔጋል ጉዞ ማማር ቁልፍ ሚናን ሊጫወቱ ይችላሉ። የተከላካይ ክፍሉ በተለይም የመሃል ተከላካዮቹ መልካም የሚባል የውድድር ዘመንን ማሳለፈቸው እንዲሁም በጣሊያኑ ታክቲሻን ማውሪዚዮ ሳሪ ስር በናፓሊ የሰለጠነው ካሊዱ ኩሊባሊ በታክቲክ አረዳድ መብሰሉ ለቴራንጋ አናብስት ተስፋ እንዲሰንቁ ያስችላቸዋል። የተደለደሉበት ምድብን ስንመለከትም ወደ ጥሎ ማለፉ ሊያሳልፋቸው የሚችሉበት ውጤት ሊያስመዘግቡ ይችላሉ። ልምድ ወሳኝ ቢሆንም የ2002 ገድል ተጨዋቾቹን ለሌላ ትልቅ ውጤት ሊያነሳሳቸው ይችላል። የ2002 ስብስብ ሩብ ፍፃሜ ድረስ ሲጓዝ በመጀመሪያ ተሳትፎው እንደነበር የሚታወስ ነው።የዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ብዛት – 2 (2002 እና 2018)የሚጠቀስ ውጤት – ሩብ ፍፃሜ (2002)ስጋትአሊዩ ሲሴ ለቡድኑ የሚሆን የጨዋታ ስልት ለማግኘት የቻለ አይመስልም። በተደጋጋሚ የቅርፅ ለውጦችን ለማምጣት መሞከሩ መልካም ቢሆንም ፍሬ አለማፍራቱ ግን አሉታዊ ጎን አለው። ይህ የሲሴን በትልቅ ውድድር ላይ የመምራት ብቃቱን ጥያቄ ምልክት ውስጥ ያስገባል። በተለያዩ ግዜያትም በታክቲካዊ ብስለቱ ላይ ጥያቄ ቢነሳም ሲሴ ከ2015 ወዲህ መሻሻሎችን ማሳየቱን ፈፅሞ መካድ አይቻልም። ቡድኑ ፈጣሪ አማካይ ይጎለዋል። ቡድኑ ባለፉት ጥቂት የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች ግብ ለማስቆጠር ተቸግሯል። ቀለል ያለች ተጋጣሚ ነች ተብላ በብዙዎች የምትገመተው ሉክሰምበርግ ላይ እንኳን ሴኔጋሎች ግብ አላስቆጠሩም። ይህ ወቅታዊ ደካማ አቋም በዓለም ዋንጫው መደገም የለበትም።*ሴኔጋል ፖላንድን በመግጠም የዓለም ዋንጫ ጉዞዋን ትጀምራለች።ሙሉ ስብስብግብ ጠባቂዎችአብዱላሂ ዲያሎ (ሬን/ፈረንሳይ)፣ አልፍሬድ ጎሜዝ (ስፓል/ጣሊያን)፣ ካዲም ንዳዬ (ሆሮያ አትሌቲክ/ጊኒ)ተከላካዮችካሊዱ ኩሊባሊ (ናፓሊ/ጣሊያን)፣ ላሚን ጋሳማ (አላንያስፓር/ቱርክ)፣ ሳሊዩ ሲስ (ቫለንሲየንስ/ፈረንሳይ)፣ ካራ ምቦዲ (አንደርሌክት/ቤልጂየም)፣ የሱፍ ሳባሊ (ቦርዶ/ፈረንሳይ)፣ዠየ ሳሊፍ ሳኔ (ሻልክ 04/ጀርመን)፣ ሙሳ ዋጉ (ዩፒን/ቤልጂየም)አማካዮችቼኮ ኮያቴ (ዌስትሃም ዩናይትድ/እንግሊዝ)፣ ኢድሪሳ ጋይ (ኤቨርተን/እንግሊዝ)፣ አልፍሬድ ንድዬ (ወልቨርሃምፕተን ዎንድረርስ/እንግሊዝ)፣ ባዱ ንዳዬ(ስቶክ ሲቲ/እንግሊዝ)፣ ቼክ ንዶዬ (በርሚንገሃም ሲቲ/እንግሊዝ)፣ እስማኤላ ሳር (ሬን/ፈረንሳይ)አጥቂዎችኬይታ ባልዴ ዲያዎ (ሞናኮ/ፈረንሳይ)፣ ማሜ ቢራም ዲዩፍ (ስቶክ ሲቲ/እንግሊዝ)፣ ሙሳ ኮናቴ (ኤሚየን/ፈረንሳይ)፣ ሳዲዮ ማኔ (ሊቨርፑል/እንግሊዝ)፣ ምባዬ ንያንግ (ቶሪኖ/ጣሊያን)፣ ዲያፍራ ሳኮ (ሬን/ፈረንሳይ)፣ ሙሳ ሶ (ቦራስፖር/ቱርክ)", "passage_id": "11773c4573eca8b346df386292691172" }, { "passage": " የተወለደው እኤአ ማርች 30/1986 በስፔኗ ሲቪያ ከተማ ልዩ ስሟ ካማስ ተብላ በምትጠራ ስፍራ ነው።አባቱ ሆዜ ማሪያ ራሞስ እናቱ ፒኩዌ ራሞስ ይባላሉ።የእግር ኳስ ህይወቱ የጀመረው የ14 ዓመት ታዳጊ እያለ ተወልዶ ያደገበት ከተማ ክለብ በሆነ ሲቪያ ነው።በ14 ዓመቱ የሲቪያ እግር ኳስ ክለብን ከተቀላቀለ በኋላ ከጊዜ ወደ ጊዜ ባሳየው እጅግ አስደናቂ አቋም እኤአ 2004 ላይ በፍጥነት ወደ ዋናው ቡድን ተሸጋገረ።ከዓመት በኋላ ክዋክብትን አድነው ወደ ቡድናቸው በመቀላቀል የተካኑት ሪያል ማድሪዶች ራሞስ እያሳየ የሚገኘውን አቋም ተከትሎ ወደ በርናባው ለማስኮብለል የሲቪያን በር ማንኳኳት ጀመሩ። በነጩ ቤት የማይሆን ነገር የለምና እንደ እኤአ በ2005 ላይ የአሁኑ የነጮቹ የጦር መሪ የቀድሞው ታዳጊ በርናባው ደረሰ።ነገር ግን በርናባው ሲደርስ ህይወት እንደጠበቀው አልሆነለትም፣ እናም የሲቪያውን ሰርጂዮ ራሞስን እውነተኛ የእግር ኳስ ክህሎት ለማየት ለአራት ዓመታት ማለትም እስከ 2009 መጠበቁ ግድ ሆነ።በወቅቱ በሎስ ብላንኮዎቹ ቤት እንደ ካፕላር ላቪራን ዴ ሊማ ፌሬራ (ፔፔ)፣ ራውል አልቢዮን፤ ኢዝጉዌል ጋራይ የመሳሰሉ የመሀል ተከላካዮች መኖራቸውን ተከትሎ ራሞስን እንደ ቀኝ ተመላላሽ ወይም መጫወቱ አማራጭ ሆነና አረፈው።ከጊዜ በኋላ እራሱን መልሶ ያገኘው አይበገሬውና ፀበኛው ተከላካይ እኤአ በ2008 ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮፓ ዋንጫ ለአገሩ ስፔን ተሰልፎ በመጫወት ከቡድን አጋሮቹ ጋር ቻምፒዮን በሆነበት አጋጣሚ ነው፡፡እንደዚህ እያለ የቀጠለው ወጣቱ ተከላካይ እያሳየ የሚገኘው አቋም እኤአ በ2010 በአህጉራችን አፍሪካ በደቡብ አፍሪካ አዘጋጅነት በተዘጋጀው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ሀገሩን ወክሎ እንዲጫወት አደረገው። በዓለም ዋንጫውም ስፔን በፍፃሜው ፍልሚያ ሆላንድን በአንድሬስ ኢኒየስታ የጭማሪ ሰአት ጎል 1-0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዓለም ቻምፒዮን ሆነች።ራሞስም ሁለተኛውን ዓለም አቀፍ ክብር ከቡድኑ ጋር ተቀዳጀ።በወቅቱ የነጮቹ ከዋክብቶች (ጋላክቲኮስ) አሰልጣኝ የነበሩት ሆዜ ሞሪኒዮ ራሞስን እንደ ቀኝ ተመላላሽ ማጫወቱን ቀጠሉበት፣ እናም ራሞስ እንደ ቀኝ ተመላላሽና ሁለገብ ተከላካይነት መጫወቱን ቀጠለ።እኤአ በ2014 የውድድር ዓመት መጀመሪያ ላይ የነጩን ቤት በትረስልጣን ከሆዜ ሞሪኒዮ የተረከቡት ጣሊያናዊው የታክቲክ ሊቅ ካርሎ አንቼሎቲ (ካርሊቶ) የራውል አልቢዮንን መልቀቅ ተከትሎ ራሞስን እንደ ቀኝ ተመላላሽ ማጫወት ጀመሩ፣ ውጤታማም ሆኑ። ከዛ ጊዜ ጀምሮም ራሞስ ቦታውን በብቃትና በአስተማማኝ ሁኔታ እየመራ ለመቀጠል ያቆመው አልነበረም።እኤአ በ2014 ጣሊያናዊው ታክቲሻን ካርሎ አንቼሎቲ የአሰልጣኝነት ሚናውን ከነጩ ቤት ሲረከቡ ከተሰጣቸው አደራ መካከል ለ12 ዓመታት ወደ ነጮቹ ካዝና ያልገባውን የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ማምጣት ነበር።በውድድር ዓመቱም ነጮቹ በሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ከወቅቱ የውድድሩ አሸናፊና እጅግ አስፈሪ ቡድን ከሆነው ከፔፕ ጋርዲዮላው ባየርሙኒክ ጋር ተገናኙ፣ አብዛኛው የእግር ኳስ ቤተሰብ የነጮቹ ቻምፒዮንስ ሊግን የማሸነፍ ህልም እዚህ ጋር እንደተቋጨ በእርግጠኝነት መናገር ጀመሩ፣ የጨዋታው ቀንም ደረሰ።እናም የመጀመሪያ ጨዋታው በግዙፍ ሳንቲያጎ በርናባው ተጀመረ፣ የማሪንጌዎቹ እህል ውሀ ‹‹በአጭሩ ተቋጭቷል›› ያስባለው የፔፕ ጋርዲዮላው ባየርሙኒክ በተደጋጋሚ ወደ ነጮቹ የግብ ክልል መድረስ ጀመረ፣ ነገር ግን በኢከር ካሲያስ ግብ ጠባቂነት፤ በሰርጂዮ ራሞስና ፔፔ የሚመራው የነጮቹ የተከላካይ ክፍል የሚቀመስ አልነበረም።ከእረፍት መልስ ጫና ፈጥረው መጫወታቸውን የቀጠሉት ባየር ሙኒኮች በተደጋጋሚ የአቻነቷን ጎል ለማስቆጠር ወደ ማሪንጌዎቹ የግብ ክልል ቢደርሱም በኢከር ካሲያስ ግብ ጠባቂነት በራሞስና ፔፔ የመሀል ተከላካይነት የሚመራው የነጮቹ የተከላካይ ክፍል አልያዝ አልቀመስ አለ፣ ጨዋታውም በነጮቹ 1-0 አሸናፊነት ተጠናቀቀ።የመልሱ ጨዋታ በአሌያንዝ አሬና መሆኑና የባየር ሙኒክ ወቅታዊ አቋም አስደናቂ መሆኑ የጨዋታው ውጤት የመቀልበስ ሰፊ እድል አለው የሚለውን ሀሳብ በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ ማግዘፉ አልቀረም።ቀኑም ደረሰና በግዙፉ የሙኒክ ስታዲየም በፖርቹጋላዊው ፔድሮ ፕሮኔካ የመሀል ዳኝነት ጨዋታው ተጀመረ።እንደተጠበቀው ሙኒኮች በተደጋጋሚ ወደ ነጮቹ የግብ ክልል ቢደርሱም የጋላክቲኮዎቹ ጠንካራ የተከላካይ ክፍል በቀላሉ በሩን የሚከፍት አልሆነም።ጨዋታው 16ኛ ደቂቃ ላይ ደረሰ፣ ክሮሺያዊው የመሀል ሜዳ ቴክኒሻን ሉካ ሞድሪች ከማዕዘን ያሻገራትን ኳስ ሰርጂዮ ራሞስ በጭንቅላቱ ገጭቶ ከመረብ አገናኛት።አራት ደቂቃዎች ተቆጠሩ፣ 20ኛ ደቂቃ ላይ አርጀንቲናዊው ኮከብ አንሄል ዲ ማሪያ ያሻገራትን ኳስ አይበገሬው ሰው ደግሞ ከመረብ አገናኛት። ጨዋታው ራሞስ ባስቆጠራቸው እንዲሁም ክርስቲያኖ ሮናልዶ ባስቆጠራት አንድ ተጨማሪ ግብ ወደ እረፍት አመራ። ከእረፍት መልስ ፖርቹጋላዊው ኮኮብ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ባስቆጠራት ተጨማሪ ግብ ነጮቹ ተስፋ እንደሌላቸው ቀደም ብሎ የተገመተውን ተጠባቂ ፍልሚያ 5ለ0 በሆነ ድምር ውጤት አሸናፊነት ወደ ፍፃሜው አሻገራቸው።በፍፃሜው ፍልሚያ ማሪንጌዎቹ ከከተማ ተቀናቃኛቸው አትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ተገናኙ።ጨዋታውም በፖርቹጋሉ ቤኒፊካ ክለብ መጫወቻ ሜዳ ስታድዮ ዳ ሉይዝ እንዲካሄድ ቀነ ቀጠሮ ተያዘለት። በነጮቹ ቤት በጉጉት የምትጠበቀዋ ቀንም ደረሰች።የ2014 የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በፖርቹጋል ስታድዮ ዳ ሉይዝ መካሄድ ጀመረ።ጠጣር የሆነ የመከላከል ስትራቴጂን የሚጠቀመው የዲያጎ ሲሚዮኒው አትሌቲኮ ማድሪድ በጋሬዝ ቤል፣ካሪም ቤንዜማ፣ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ከሚመራው የነጮቹ የፊት መስመር የሚደርስበትን ጫና በመቋቋም 36ኛው ደቂቃ ላይ በመልሶ ማጥቃት ኡራጓዊው ዲያጎ ጎዲን ለአትሌቲኮዎች ባስቆጠረው ግብ ጨዋታው ወደ እረፍት አመራ።ከረፍት መልስ ማሪንጌዎቹ ያላቸውን ሀይል ሁሉ ተጠቅመው የአቻነቷን ጎል ለማስቆጠር ቢጥሩም የአትሌቲኮ ማድሪድ ተከላካዮች በቀላሉ እጅ የሚሰጡ አልሆኑም።ጨዋታውም እንዲህ እንዲህ እያለ ወደ መገባደጃው ደረሰ።ደቂቃው እየነጎደ በሄደ ቁጥር በነጮቹ ደጋፊዎች ብሎም ተጫዋቾች ውጥረትና ሀዘን ነገሰ፣ ሙሉ ዘጠና ደቂቃው አልቆ ጭማሪ ደቂቃ ተጨመረ፡፡አንሄል ዲ ማሪያ በግራ በኩል ያሻማትን ኳስ ቶቢ አልደርዌሪልድን በመንካቷ የመዓዘን ምት ለሪያል ማድሪድ ተሰጠ።ሉካ ሞድሪች የማዕዘን ምቱን ለማሻማት ወደ ሜዳው ጠርዝ አመራ።የአትሌቲኮ ማድሪድ ደጋፊዎች፣ የአሰልጣኞች፣ ተጫዋቾችና የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች የጨዋታውን መጠናቀቅ የምታውጀውን የዳኛውን ፊሽካ ለመስማት ጉጉታቸው ከጆሯቸው አልፎ በፊት ገፅቸው ይነበበ ጀመረ፡፡ሞድሪች የማዕዘን ምቱን አሻማ።ቅዠት በሚመስል መልኩ የነጮቹ የቁርጥ ቀን ደራሽ ሰርጂዮ ራሞስ ጋርሲያ ኳሷን የአትሌቲኮ ማድሪድ መረብ ላይ ዶላት።ስታድዮ ዳ ሉይዝ በሪያል ማድሪድ ደጋፊዎች ደስታ በአትሌቲኮ ማድሪድ ደጋፊዎች ድንጋጤና መሪር ሀዘን ተዋጠች።ከሰከንዶች በፊት ሪያል\nማድሪድ ዜሮ አትሌቲኮ\nማድሪድ አንድ ይል\nየነበረው የውጤት መግለጫ\nስክሪን በቅፅበት 1-1 በሚል\nውጤት አወጀ።ጨዋታውም ወደ\nጭማሪ ደቂቃ አመራ።ከዚያም\nበኋላ የጨዋታው መልክ\nተቀየረ።ዌልሳዊው ኮከብ ጋሬት\nቤል፣ ማርሴሎ ቪዬራና\nሮናልዶ ባስቆጠሯቸው የጭማሪ\nሰዓት ግቦች ተጠባቂው\nጨዋታ በማሪንጌዎቹ 4ለ1\nአሸናፊነት ተጠናቀቀ። ለ12\nዓመታት ወደ በርናባው\nያልደረሰው ባለትልቅ ጆሮው\nዋንጫም ወደ በርናባው\nተመለሰ።ራሞስም እንደ መሀል\nተከላካይነት መጫወት በጀመረ\nበመጀመሪያ ዓመቱ የአውሮፓ\nቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን\nለመሳም በቃ።አዲስ ዘመን ጥር 17 ቀን 2012 ዓ.ም ቦጋለ አበበ", "passage_id": "68fd3c1220513dbf63d98cd7a416a576" }, { "passage": "ብራዚላውያን እግር ኳስን ማምለክ ብቻ ሳይሆን ከማንም በላይ አስንቀው መጫወትንም አሳምረው ያውቁበታል፡፡እስካሁን ድረስ በተካሄዱት የአለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድሮች ውስጥ አለማችን እንደ ብራዚል አምስት ጊዜ አሸንፎ የአለም ሻምፒዮን የሆነ ሌላ ሀገር የላትም፡፡ ብራዚላውያን እንደ ጨዋታው ሁሉ በአለማችን አቻ የለውም ለሚባለው የእግር ኳስ ቡድናቸውና ለሀገር ውስጥ ሊጋቸው ያላቸው ትኩረትና ድጋፍም ዲካ የለሽ ነው፡፡ኢትዮጵያውያንም በእግር ኳስ ጨዋታ ፍቅር ያበዱ ተብለው ጐራ ከተለየላቸው ህዝቦች አንዱ ናቸው፡፡ ነገሩ እውነት ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን እግር ኳስ ጨዋታን ይወዳሉ፡፡ ይህ አገላለጽ ያንሳል ከተባለም “ያፈቅራሉ” ተብሎ ሊነገርላቸው ይችላል፡፡ ኢትዮጵያውያን እንደብራዚላውያን እግር ኳስን አያመልኩትም፡፡ እንደ ብራዚላውያን በአለምአቀፍም ሆነ በአህጉራዊ ትልልቅ ውድድሮች በተደጋጋሚ አሸንፎ ሻምፒዮን የሆነ የእግር ኳስ ቡድንም የላቸውም፡፡ለኢትዮጵያውያን እንዲህ ያለውን ብሔራዊ ክብር የሚያጐናጽፏቸው ሯጮቻቸው ናቸው፡፡ አስደናቂዎቹ አትሌቶቻቸው በተለያዩ አለማቀፋዊና አህጉራዊ ውድድሮች ላይ በተደጋጋሚ በማሸነፍ፣ የድል አድራጊነትን ልዩ ክብር ለረጅም አመታት አስለምደዋቸዋል፡፡ኢትዮጵያውያን በእግር ኳስ ፍቅር ያበዱ ናቸው ይባሉ እንጂ ጨርቃቸውን ያስጣላቸው የሀገራቸው የእግር ኳስ ሊግ ሳይሆን የአውሮፓ ሊጐች፣ በተለይም የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ነው፡፡ ለሀገራቸው ውድድር ያላቸው ትኩረትና ድጋፍም እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ ከሀገራቸው እግር ኳስ እድገት ይልቅ እረፍት ነስቶ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያስጨንቃቸው የእንግሊዝ አርሴናል ክለብ ለበርካታ አመታት ከሻምፒዮንነት መራቁ ወይም ማንቸስተር ዩናይትድ ሃያልነቱን በከተማው ተቀናቃኝ ክለብ በማንቸስተር ሲቲ ይነጠቅ ይሆን የሚለው ጉዳይ ነው፡፡የኢትዮጵያውያኑ ይህ ታላቅ “ጭንቀት” ለረጅም አመታት የድል ጽዋ ሲያቃምሳቸው ከኖረውና የብሔራዊ ኩራታቸው ምንጭ ከሆነው የአትሌቲክስ ስፖርታቸውም በላይ ነው፡፡ ለኢትዮጵያውያን የስፖርት የሚዲያ ባለሙያዎች የቅድሚያ ትኩረታቸው የአትሌቶቻቸው የማሸነፍ ዜና ወይም ጠቅላላ የአትሌቲክስ ጉዳይ ሳይሆን የቸልሲ ወይም የሊቨርፑል መሸነፍ አሊያም ነጥብ መጣል ነው፡፡በአውሮፓ አሁን ወቅቱ የበጋው ጊዜ ሊገባ እያኮበኮበ ነው፡፡ ሁሉም የአውሮፓ የእግር ኳስ ሊጐችም የአመቱን ውድድራቸውን አጠናቀው፣ ለቀጣዩ የውድድር ወቅት በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያውያኑም ሆኑ ጠቅላላ የስፖርት ሚዲያ ባለሙያዎቻቸው ቀልባቸውንና ልባቸውን የሚስብና በየቀኑ ለተደጋጋሚ ጊዜ የሚያቀርቡት የአውሮፓ እግር ኳስ ሊግ ወሬ እንደልባቸው ማግኘት አይችሉም፡፡የአውሮፓውያኑን የእግር ኳስ ሊግ በተለይ ደግሞ የእንግሊዝን ፕሪምየር ሊግ በሳተላይት ቴሌቪዥን በመከታተል፣ ስለ እግር ኳስ ጨዋታ አሠለጣጠንና የተጨዋቾች አሠላለፍ ዘዴ፣ እንደማንቸስተር ዩናይትድ አሠልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርግሰን የመሳሰሉትን አንጋፋና ውጤታማ አሠልጣኞችን በመተቸትና ሙያቸውን እንዲያሻሽሉ ምክር በመለገስ ረገድ የየትኛውም ሀገር ዜጋ ቢሆን ኢትዮጵያውያኑን በተለይም የስፖርት የሚዲያ ባለሙያዎችን መወዳደር አይችልም፡፡በኢትዮጵያ ከስሩ ሰዎች ሠባቱ የአውሮፓ የእግር ኳስ ሊግ የተዋጣላቸው ተንታኞች ናቸው ቢባል አነሱ ካልሆነ በቀር አጋነናችሁት ብሎ የሚቀየም አይኖርም፡፡አሁን የአውሮፓን ብቻ ሳይሆን የመላውን አለም የስፖርት ትኩረት የተቆጣጠረው የለንደን ኦሎምፒክ ነው፡፡ የኦሎምፒክ ውድድሮችን በማዘጋጀት የእንግሊዟ ለንደን ከተማ “ሀትሪክ (ሶስቴ) የሠራችበት የ2012 ዓ.ም 31ኛው የለንደን ኦሎምፒክ ሊጀመር ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል፡፡ ኢትዮጵያውያኑም ለጊዜውም ቢሆን የስፖርት ትኩረታቸውን ወደዚህ ኦሎምፒክና የአትሌቲክስ ቡድናቸው ማስመዝገብ በሚችለው ውጤት ላይ ለማድረግ ተገደዋል፡፡የኢትዮጵያን ድንበር የደቡብ ወሰን ተሻግሮ ቁልቁል ሲኬድ ጐረቤቷ ኬንያ ትገኛለች፡፡ ኬንያውያን እንደ ጐረቤቶቻቸው ኢትዮጵያውያን በእግር ኳስ ፍቅር ያበዱ ናቸው ብሎ ማንም አፉን ሞልቶ መናገር አይችልም፡፡ እግር ኳስን በተመለከተ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ ኬንያውያንም በአለም አቀፍ ውድድሮች ተካፍሎ ሻምፒዮን የሆነ የእግር ኳስ ቡድን ኖሮዋት እንደማያውቅ ግን በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡ ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በተለያዩ አለማቀፋዊና አህጉራዊ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ተደጋጋሚ ድሎችን በመጐናፀፍ የብሔራዊ ኩራት ምንጮቻቸው ዝነኛ አትሌቶቻቸው ናቸው፡፡ በዚህ በአትሌቲክስ ስፖርት ከኢትዮጵያውያን በተቃራኒው የሚያቆማቸው አንድ ጉዳይ ለመላው ኬንያውያንም ሆነ ለስፖርት ሚዲያ ባለሙያዎቻቸው የአትሌቶቻቸው የድል ዜናም ሆነ ሌላው አትሌቲክስ ነክ የሆነው ነገር ከሁሉም የላቀ የትኩረት አጀንዳቸው መሆኑ ነው፡፡ለብራዚላውያንና አርጀንቲናውያን የእግር ኳስ ጨዋታ ”ዋነኛው ፊታውራሪ እኔ ነኝ!” የሚል የፉክክር ምንጭ ነው፡፡አሜሪካንና ጃማይካን በጥብቅ የሚያፎካክራቸው ነገር አለ ከተባለም የአጭር ርቀት የአትሌቲክስ ውድድር ነው፡፡ የአለም ፈጣኑ ሰው የሚል የክብር መጠሪያ በማግኘት ለበርካታ አመታት የአሜሪካና የጃማይካ አትሌቶች የአጭር ርቀት የአትሌቲክስ ውድድርን እየተፈራረቁ ነግሰውበታል፡፡ኬንያ ከእንግሊዝ ቅኝ አገዛዝ ነፃ ወጥታ እንደ ሉአላዊት አገር ከቆመችበት ከ1963 ዓ.ም ጀምሮ ለክፉ የሚሰጥ ነፋስ ሳይነፍስባት፣ ከኢትዮጵያ ጋር በመልካም ጉርብትናና ወዳጅነት እየኖረች ያለች ሀገር ናት፡፡ በመካከላቸው ለረጅም ዘመናት የዘለቀው ሠላማዊ ጉርብትናቸው ዋነኛ መሠረቱ ወንድማማችነትና የጋራ ትብብር ነው፡፡ ነገር ግን በኢትዮጵያና በኬንያ መካከል ለበላይነት የሚደረግ ከፍተኛ ፉክክር አለ ከተባለ የዚህን ፉክክር ምንጭ የምናገኘው ከጦር ሀይል ጉልበታቸው ጨርሶ አይደለም፡፡ ይልቁንስ ከሠላማዊው የስፖርት መድረክ ብቻ ነው፡፡ የሁለቱን ሀገራት ብቸኛ የሃያልነት ፉክክር የምናገኘው በረጅም ርቀት የሩጫ ውድድር ነው፡፡ የአለምን የአጭር ርቀት የሩጫ ውድድር አሜሪካና ጃማይካ እንደነገሱበት ሁሉ፣ ካለፉት ሠላሳና አርባ አመታት ወዲህ የረጅም ርቀት የሩጫ ወድድርን እንደ ኢትዮጵያና ኬንያ በበላይነት መቆጣጠር የቻለ አንድም ሀገር በአለማችን ጨርሶ አልታየም፡፡ለረጅም ዘመናት በአለም አቀፍ ደረጃ በተካሄዱ የረጅም ርቀት ውድድሮች የአሸናፊነት የግምት ርዕስ የሚሆነው ከኢትዮጵያና ከኬንያ ማን ያሸንፋል የሚለው ብቻ ነው፡፡ የሌላው ሀገር በተለይ ደግሞ የአውሮፓና የአሜሪካ ተወዳዳሪዎች ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዜግነታቸውን ቀይረው ለአውሮፓና ለአሜሪካ ከሚወዳደሩት እንደ ሞ ፋራህ አይነት ካልሆኑ በቀር፣ ለዚህ የአሸናፊነት ግምት የመታጨት እድላቸው በእጅጉ ያነሰና ሲያጋጥምም እንደ ብርቅ የሚታይ ነው፡፡በዚህ የተነሳም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የአሸናፊነትና የበላይነት የፉክክር ስሜት ከፍተኛ ነው፡፡ በኬንያውያን ላይ መጠኑ ልቆ ይታያል እንጂ ሁለቱም ሀገራት አንዳቸው በአንዳቸው መሸነፉን በጣም ይጠሉታል፡፡ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ የፉክክር ስሜት በሁለቱ ሀገራት ላይ መመልከት የምንችለው በከፍተኛ አለምአቀፋዊ ውድድሮች ላይ ነው፡፡ እነሆ አሁን ሃያ ስድስተኛው የለንደን ኦሎምፒክ እየተካሄደ የሚገኝበት ጊዜ ነው፡፡ እናም ይህ ኦሎምፒክ ተጠናቆ ማንኛቸው በበላይነት እንደሚያሸንፉ እስኪታወቅ ድረስ ለኢትዮጵያም ሆነ ለኬንያ አስደሳቹንና ሠላማዊውን የበላይነት የፉክክር መንፈስ እንደገና ይዞላቸው መጥቷል፡፡የሚያሳጣ ምናልባትም በአጭር ጊዜ ውስጥ ችሎታውን ውድድሮችን በማሸነፍ ማስመስከር ለሚችል ወጣትና ተስፈኛ አትሌት፣ በኢትዮጵያና በኬንያ የስምንት መቶና የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር፣ የሶስት ሺ ሜትር መሠናክል፣ የአምስት ሺ የአስር ሺ ሜትርና የማራቶን ሯጮች ቡድን ውስጥ አባል ለመሆን ከመቻል ይልቅ በግሉ ተወዳድሮ የኦሎምፒክ ሜዳሊያ ተሸላሚ ለመሆን የበለጠ እድል ሊኖረው ይችላል፡፡ኬንያዊው ፓትሪክ ማካው፤ ባለፈው መስከረም ላይ የተደረገውን የማራቶን ውድድር ያሸነፈው በኢትዮጵያዊው ዘመን አይሽሬ ታላቅ ሯጭ ሀይሌ ገብረስላሴ ተይዞ የቆየውን የማራቶን ሪከርድ በመስበርና ሁለት ሰአት ከሶስት ደቂቃ ከሠላሳ ስምንት ሰኮንድ አዲስ ሰአት በማስመዝገብ ነው፡፡ ፓትሪክ ማካው ያስመዘገበው ይህ የማራቶን ድል ለኬንያውያን ቶርታ ኬክ ከእነ ክሬሙና ስትሮው ቤሪው አይነት ነበር፡፡ ተራ ሳይሆን ድርብርብ ድል ነበር፡፡ ውድድሩን ማሸነፍ አዲስ የማራቶን ሪከርድ ማስመዝገብ፡፡ ያሸነፉትና ሪከርዱንም የሠበሩበት የዋነኛ ተፎካካሪያቸውን የኢትዮጵያ አትሌቶች በማሸነፍ፡፡ይህን ድርብርብ ድል ያስጠገባቸው የአለም ቁጥር አንድ የማራቶን ሯጫቸው ፓትሪክ ማካው ግን በለንደን ኦሎምፒክ የሚወዳደረው የኬንያ የማራቶን ቡድን አባል መሆን አልቻለም፡፡ ይህ የሆነው የኬንያ የአትሌቲክስ ቡድን አሠልጣኞች በጥላቻ አሊያም በሙስና ወይም በሆነ በሌላ ምክንያት የማራቶን ቡድኑ አባል እንዳይሆን ስላደረጉት አይደለም፡፡ የቡድኑ አባል ሆኖ እንዳይመረጥ ሰበብ ሊሆን የሚችል የጤና እክል ገጥሞት ስለተጐዳም ጨርሶ አይደለም፡፡ “እንዴ! ፓትሪክ ማካው እኮ የአለምን የማራቶን ሩጫ ሪከርድ በመስበር መቆጣጠር የቻለ ቁጥር አንድ ሯጭ ነው፡፡ ይህን እንኳን የሀገሩ ልጆች ኬንያውያን ይቅርና መላው አለም ጠንቅቆ ያውቀዋል፡፡ የወቅቱ እውነታ ግን ከዚህ ሀገራዊም ሆነ አለማቀፋዊ እውነታና ዝና በእጅጉ የተለየ ነው፡፡ማንም ከኬንያ የኦሎምፒክ የማራቶን ሩጫ ቡድን አባላት ውስጥ የአለማችንን ቁጥር አንድ የማራቶን ሯጭ የፓትሪክ ማካውን ስም ማግኘት አይችልም፡፡ ምናልባት ለመናገር ወይም ፈታ ብሎ ጉዳዩን ለማስረዳትና ሌሎችን ለማሳመን አስቸጋሪ ነው ካልተባለ በቀር ፓትሪክ ማካውን ከቡድኑ ውስጥ ማግኘት ያልተቻለበት ምክንያት አንድና አንድ ብቻ ነው፡፡ የማራቶን ቡድኑ አባላት መሆን የሚችሉትን ምርጥ ሯጮች ለመምረጥ የተደረገውን ውድድር ፓትሪክ ማካው ማሸነፍ አቃተው፡፡የለም! ማሸነፍ አቃተው የሚለው ቃል የነገሩን ሙሉ ስዕል አይገልፀውም፡፡በዚያ ውድድር ፓትሪክ ማካው ያቃተው ማሸነፍ አይደለም፡፡ ስድስተኛ ሆኖ ነው የጨረሰው፡፡ የአለማችን ቁጥር አንድ ማራቶነኛ፤ አዲስና ወጣት የማራቶን ሯጭ የሀገሩን ልጆች ጨርሶ መቋቋም ሳይችል ቀረ፡፡ በዚህም በኬንያም ሆነ በአለም አዲስ ታሪክ ዳግመኛ ለማስመዝገብ በቃ፡፡ ፓትሪስ ማካው የአለም የማራቶን ሪከርድ ባለቤት ሆኖ ለሀገሩ ብሔራዊ ቡድን መሰለፍ ያልቻለ፣ የመጀመሪያው አሳዛኝ የማራቶን ሯጭ ሆነ፡፡አልጋ ወራሹ ሯጭ እያሉ በአድናቆትና በፍቅር ስለሚያሞኻሹት ቀነኒሳ በቀለ ለኢትዮጵያውያን መናገር አንድም ለቀባሪው እንደማርዳት አሊያም ስለሀገራቸው ድንቅ አትሌት ባይተዋርና እንግዳ እንደሆኑ አድርጐ እንደመቁጠር ተደርጐ ሊወስድ ይችላል፡፡ ቀነኒሳ በቀለ ከአራት አመት በፊት በቤጂይንግ ቻይና በተካሄደው ኦሎምፒክ፣ በአምስትና በአስር ሺ ሜትር የሩጫ ውድድር መላ አለምን አጀብ ባስባለ ድንቅ ብቃት በማሸነፍ፣ ሀገሩን የሁለት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት እንድትሆን ለማድረግ ችሏል፡፡ በቀነኒሳ ድርብ ድል የተነሳም በዓለም ታላቅ የውድድር አደባባይ ላይ ብሔራዊ መዝሙራቸው እየተዘመረ፣ ከሁሉም ነገር በላይ ፍቅርና ክብር የሚሰጡት ብሔራዊ ባንዲራቸው ከፍ ብሎ ሲሰቀል የተመለከቱት ኢትዮጵያውያን፤ ወደር በሌለው ብሔራዊ የኩራት ስሜት ተውጠው የደስታና የድል አድራጊነት ሲቃ የሚፈጥረውን እንባ አንብተዋል፡፡የዝነኛውን አትሌት የቀነኒሳ በቀለን አለማቀፋዊ ገድል ማንም ቢሆን በቀላል ማስታወሻ ዘርዝሮ ለማስረዳት ይቸገራል፡፡ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ “አልጋ ወራሹ” እያሉ የሚጠሩት ከቶውኑ ያለነገር አይደለም፡፡ በኦሎምፒክ የሁለት ወርቅ ሜዳሊያ ድርብ ድል ባለቤት በሆነበት የአምስት ሺና የአስር ሺ ሜትር ሩጫ ግን ዘውዱን ከመጀመሪያው ንጉስ ከሀይሌ ገብረስላሴ ተቀብሎ ከደፋና ከነገሠ ቆይቷል፡፡ የእነኝህ ርቀቶች የአለም ሪከርድ ባለቤትነት የተያዘውም በእርሱ ነው፡፡ይሁን እንጂ በኢትዮጵያና በኬንያ የመካከለኛና የረጅም ርቀት ሩጫ የብሔራዊ ቡድን ውስጥ በአባልነት ለመካተት ያለውን ከፍተኛ ትግልና ፉክክር ለማሳየት ቀነኒሳ በቀለ ሌላ ተጨማሪ አብነት መሆን ይችላል፡፡ የሁለቱም ርቀቶች ንጉስና የአለም ሪከርድ ባለቤት የሆነው ቀነኒሳ በቀለ፤ በኦሎምፒክ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባል መሆን የቻለው በአስር ሺ ሜትር ቡድን ውስጥ ብቻ ነው፡፡ በአምስት ሺ ሜትር ቡድኑ ውስጥ ለቀነኒሳ በቀለ የሚሆን ቦታ የለም፡፡ የሱን ቦታ ከእሱ የበለጠ ብቃት ያለው አትሌት ይዞታል፡፡በአምስት ሺና በአስር ሺ ሜትር ታላላቅ አለምአቀፍ ውድድሮች መላ አለምን በከፍተኛ ሁኔታ ባስደነቀ ተአምራዊ ብቃት በተደጋጋሚ ጊዜ በማሸነፍ፣ የሀገሯ ስምና ዝና በአለም አደባባይ እንዲልቅ ማድረግ የቻለችውን ድንቋን አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን፤ ኢትዮጵያውያን የሀገሯ ልጆች “ጥሩዬ” በሚል አጭር የፍቅር የቁልምጫ ስም ይጠሯታል፡፡ ጥሩነሽ ግን ከጥሩም በላይ ናት፡፡ ጥሩነሽ እጅግ ድንቅና አይበገሬ “World class” አትሌት ናት፡፡ እንደ ቀነኒሳ በቀለ ሁሉ በቤጂይንግ ኦሎምፒክ ልዕልት በሆነችበት በአምስት ሺና በአስር ሺ ሜትር ሩጫ በማሸነፍ የሁለት ወርቅ ሜዳሊያ ድርብ ድል ባለቤት መሆን ችላለች፡፡ይህ የኦሎምፒክ ድርብ ድሏ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካም ድል ነው፡፡ በአንድ ኦሎምፒክ በሁለት የረጅም ርቀት የሩጫ ውድድር ላይ በማሸነፍ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት መሆን የቻለች አፍሪካዊት አትሌት፤ የሀገሬ ባለቅኔ “ነገር የገባት ሰጐን” ብሎ ቅኔ የተቀኘላት “ጥሩዬ” ብቻ ናት፡፡እንዲህ የለ ዘመን የማይሽረው ታሪክ ባለቤትና የአምስት ሺህና የአስር ሺ ሜትር ሩጫ ውድድር ንግስት የሆነችውን ድንቅ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን፤ በኦሎምፒክ ተሳታፊ ከሆነው የሀገሯ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ከአስር ሺ ሜትር የተወዳዳሪዎች ቡድን ውስጥ ብቻ ነው፡፡ እንግዲህ በሚወዳደሩባቸው ርቀቶች የአለም ቁጥር አንድ የሆኑት እነ ማካው፣ ቀነኒሳና ጥሩነሽ በሚጠበቅባቸው ሁሉ መወዳደር አለመቻላቸው፣ በኢትዮጵያና በኬንያ የኦሎምፒክ ቡድን ውስጥ አባል ሆኖ ለመመረጥ ያለው ፉክክር ምን ያህል ፈታኝ መሆኑን ያሳያል፡፡ አሁን ትልቁን ጥያቄ እንጠይቅ፡፡ ይህን የረጅም ርቀት የአትሌቲክስ ውድድር እነዚህ ሁለት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ብቻ በበላይነት መቆጣጠር የቻሉበት ምስጢር ምንድነው?ይህን ጥያቄ ለመመለስ የተለያዩ ባለሙያዎች የተለያዩ ምክንያቶችን አቅርበዋል፡፡ ኢትዮጵያና ኬንያ ያላቸው የጂኦግራፊ አቀማመጥ፣ የኢትዮጵያውያንና የኬንያውያን የተፈጥሮ ዘረመል፣ ለስኬታቸው ዋና መሠረት ነው ይላሉ፡፡ ሌሎቹ ባለሙያዎች ደግሞ የአትሌቶቹን አሯሯጥና ያደጉበትን ሁኔታ በማጥናት፣ ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን አትሌቶችን በረጅም ርቀት የሩጫ ውድድር የአለም ቁንጮ ያደረጋቸው የኑሮ ሁኔታዎችና ሌሎች ማህበራዊ ምክንያቶች ናቸው በማለት ያስረዳሉ፡፡ ሀይሌ ገብረስላሴ አንድ እጁን ወደ ደረቱ አስጠግቶ የሚሮጠውን አሯሯጡንና ከብቶችን ለማገድም ሆነ ውሃ ለመቅዳት ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን ወጣቶች በየእለቱ በሩጫ የሚያሳልፉትን ጊዜና የሚሸፍኑትን ረጅም ርቀት ለዚህ ምክንያታቸው እንደ አብነት አድርገው ይጠቅሳሉ፡፡ምስጢሩን ለማወቅ የሚደረገው ጥረትና ምርምር ግን አላቆመም፡፡ የኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን በረጅም ርቀት ሩጫ እያሸነፉ አለምንና ተማራማሪዎችን ማስደመማቸውም እንዲሁ፡፡ ለንደንም ተረኛ የንግስና ከተማቸው ለመሆን እነሆ አማልክት እድሉን ሰጥተዋታል፡፡  ", "passage_id": "6b3e7589af174b6ba6fb8856f922864c" }, { "passage": "ቻይና፣ ህንድ፣ ኢንዶኔዢያ ለእግር ኳስ ባይተዋር ናቸውበአሜሪካ ክቧ ኳስ ከሞላላ ኳስ ጋር መፎካከር አልቻለችምየህንድ ቡድን በአለም ዋንጫ የመካፈል ጥሩ እድል ያገኘው ከ64 አመታት በፊት ነው። በብራዚል በተዘጋጀው የያኔው የአለም ዋንጫ ላይ ያለ ማጣሪያ እንዲካፈል የተጋበዘው የህንድ ቡድን፣ እድሉን አልተጠቀመበትም - በሁለት ምክንያቶች። አንደኛው ምክንያት፣ ድህነት ነው። የመጓጓዣና የመሰንበቻው ወጪ ከበዳቸው። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ኋላቀርነት ነው። የህንድ ቡድን የፊፋን ህግ ለማክበር አልፈለጉም - ያለ ጫማ ነው የምንጫወተው በማለት። ጫማ ካደረግን፣ ጥቃቅን ነፍሳትን ረጋግጠን ልንገድል እንችላለን ብለው የሰጉት የህንድ ተጫዋቾች፤ ሃጥያት ውስጥ መግባት አንፈልግም ብለው ከአለም ዋንጫ ቀርተዋል። እንዲህ፣ ተረት የሚመስል ኋላቀር ባህል ምን ይባላል?ቻይናን ጉድ ያደረጋት ግን፣ ጥንታዊ ባህል አይደለም። ለነገሩማ፣ እግር ኳስ የሚመስል ጨዋታ የተጀመረው በጥንታዊ ቻይና እንደሆነ ይነገር የለ! ቻይናዊያን ከእግር ኳስ ጋር የተራራቁት በኮሙኒዝም ምክንያት ነው። የድሮዎች የአገራችን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ እነ ደርግና እነ ኢህአፓ ጭምር በአድናቆት የዘመሩላቸው የቻይና መሪ ማኦ ዜዱንግ፣ አገሬውን ሁሉ ሌት ተቀን ፋታ በማይሰጥ ስብሰባ፣ ግምገማና የስራ ዘመቻ ወጥረው ነበር የያዙት። ኳስ ለመጫወት ጊዜ አልነበረም። ስብሰባውና የስራ ዘመቻውም ጠብ የሚል ነገር አልተገኘበትም - 20 ሚሊዮን ቻይናዊያን በረሃብ ያለቁት በማኦ ዘመን ነው። ከማኦ በኋላ፣ በዴንግ ዚያዎፒንግ ዘመን በመንግስት ተተብትቦ የቆየው ኢኮኖሚ ለግል ኢንቨስትመንት ሲከፈት፣ ከዚያም ሲስፋፋ አገሪቱ በፍጥነት ወደ እድገት መጓዝ ጀምራለች። በመንግስት የተተበተበው ፖለቲካ ግን ብዙም አልተቀየረም። ያለ መንግስት ፈቃድ ከ10 በላይ ሰዎች በአንድ ቦታ ቢሰባሰቡ ይታሰራሉ። ክልክል ነው። የሰፈር ወጣቶች እግር ኳስ ለመጫወት በየቀኑ ቀበሌና ወረዳ ሊቀመንበር ጋ እየሄዱ የፈቃድ ማመልከቻ ሲያስገቡ ይታያችሁ። “ስፖርት ለአገር ልማትና ለጤናማ ህብረተሰብ ወሳኝ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ይታወቃል። እኛ ስማችን ከዚህ በታች የተዘረዘረ የሰፈር ወጣቶች፣ ለአገርና ለህብረተሰብ ልማት በማሰብ ዛሬ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት እግር ኳስ ለመጫወት አስበናል። ፅ/ቤቱ ፈቃድ እንዲሰጠን እየጠየቅን፣ ለሚደረግልን ትብብር አብዮታዊ ምስጋና እናቀርባለን...”  “አብዮት ወይም ሞት!” በሚል መፈክር የታጀበ ማመልከቻ እየፃፉ እግር ኳስ ለመጫወት የሚጓጓ ብዙ ወጣት አይኖርም። በኮሙኒዝም የተሽመደመደው  የቻይና እግር ኳስ፤ እስከዛሬ ገና ቆሞ የመራመድ ብርታት አላገኘም። ደግነቱ፣ እንደ ታሊባን ወይም እንደ አልሸባብ የእግር ኳስ ጨዋታ በቲቪ መመልከት አልተከለከለም። ብዙ ቻይናዊያን እግር ኳስ ባይጫወቱም፣ መመልከት ግን ይወዳሉ። 300 ሚሊዮን ቻይናዊያን በ2010 የአለም ዋንጫ ውድድሮችን በቲቪ ተከታትለዋል።ህንድና ቻይና ከእግር ኳስ አለም የራቁት በጥንታዊ ኋላቀር ባህልና አኮራምቶ በሚተበትብ የኮሙኒዝም አፈና ሳቢያ ከሆነ፤ አሜሪካ ከእግር ኳስ ጋር ያልተወዳጀችው በምን ምክንያት ይሆን? በሌሎች ተወዳጅ ስፖርቶች ምክንያት ነው። በአሜሪካ ስቴዲየም የሚገባ ብዙ ተመልካች የሚሰበሰበው በሞላላ ኳስ የሚካሄደውን ጨዋታ ለማየት ነው። በአማካይ በእያንዳንዱ ጨዋታ ከ68ሺ በላይ ተመልካች ስቴዲየም ይገባል - ያንን ነው ፉትቦል የሚሉት። እግር ኳስን፣ ሶከር እያሉ ነው የሚጠሩት። ከዚያ በኋላ ደግሞ ቤዝ ቦል አለ። የቤዝ ቦል ጨዋታ ለመመልከት በአማካይ ከ30ሺ በላይ ሰው ስቴዲየም ይገባል። እግር ኳስ ለማየት የሚሰበሰበው ተመልካች፣ ከቅርጫት ኳስ ተመልካቾች ቁጥር ብዙም አይራራቅም - በአማካይ 18ሺ ገደማ ሰው።በአጭሩ፤ አውሮፓን፣ ደቡብ አሜሪካንና አፍሪካን ያጥለቀለቀው የእግር ኳስ ዝና፣ በአሜሪካ ገና አልተስፋፋም። እንዲያም ሆኖ፣ ከሌሎቹ ትልልቅ አገራት (ከህንድ እና ከቻይና )ጋር ሲነፃፀር፣ የአሜሪካ ሳይሻል አይቀርም። የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን በተደጋጋሚ በአለም ዋንጫ ላይ ሲሳተፍ እያየን አይደል? ሶስቱ ትልልቅ አገራት፤ (ህንድ፣ ቻይና እና ኢንዶኔዢያ) ግን፤ ለአለም ዋንጫ ባይተዋር ናቸው። በእርግጥ፤ ቻይና አንዴ በአለም ዋንጫ ተሳትፋለች። ግን፤ እንደተሳተፈች አይቆጠርም። የቻይና ቡድን አንድም ጊዜ አላሸነፈም። ጨርሶ፣ አንድም ጎል ሳያስገባ ነው በመጀመሪያው ዙር ከውድድሩ የተሰናበተው። እግር ኳስ ለማየት ወደ ስቴዲየም ጎራ ማለት፤ በህንድ፣ በኢንዶኔዢያና በቻይና ገና አልተለመደም።በዚህ በዚህ ጀርመንን የሚስተካከል የለም። በእያንዳንዱ የቡንደስ ሊጋ ጨዋታ በአማካይ 42ሺ ተመልካች ስቴዲየም ይገባል። በእንግሊዙ ፕሪሚየር ሊግ ደግሞ፣ 36ሺ ሰዎች ስቴዲየም ይታደማሉ። በቅርቡ የተጠናቀቀውን የፕሪሚየር ሊግ ለማየት በድምሩ 14 ሚ. ገደማ ቲኬቶች ተሽጠዋል።", "passage_id": "01ac1a8e6385d48282f2f7a1d3bcdbee" } ]
06c13cdd6749ad9b64c1d091309c1493
e69e93f180f59c3569cf0cb2bbc302a6
የኦሎምፒክ ተሳትፎ ያልተሳካለት ብሄራዊ ቡድን
ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ መድረክ በብዛት ተሳታፊ ከሆነችባቸው የአትሌቲክስና ብስክሌት ስፖርቶች በመቀጠል ይጠቀሳል፤ ቦክስ፡፡ በቦክስ ስፖርት የመጀመሪያው የኦሊምፒክ መድረክ ተሳትፎ እአአ በ1968 በተካሄደው የሜክሲኮ ኦሊምፒክ ሲሆን፤ በወቅቱም አራት ቦክሰኞች ተካፋይ ነበሩ። ከዚያ በኃላ በተካሄዱ ስምንት ኦሊምፒኮች ላይም ሃገሪቷ ስፖርተኞቿን ማሳተፏን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን መረጃ ይጠቁማል፡፡ በመድረኩ ለመጨረሻው ተሳትፎ ካደረገችበት እአአ የ2008 ቤጂንግ ኦሊምፒክ በኋላም ተሳታፊ የሚያደርጋትን እድል ሳታገኝ በመቅረቷ ኢትዮጵያ በስፖርቱ አልተወከለችም፡፡ ከወራት በኋላ ጃፓን በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ የአዘጋጅነት እድሉን ባገኘችበት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ላይም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፤ ከአትሌቲክስ፣ ብስክሌት፣ ቴኳንዶ እና የውሃ ዋና ስፖርቶች በተጓዳኝ ተሳታፊ ለመሆን ያቀደበት ሌላኛው ስፖርት ቦክስ ነበር፡፡ ለእቅዱ መሳካት ይረዳ ዘንድም በማጣሪያ ውድድር ላይ ብሄራዊ ቡድኑ ተካፋይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በሴኔጋሏ ዳካር አስተናጋጅነት በተካሄደው በዚህ ቻምፒዮና ላይም ስድስት ወንድ እና አንዲት ሴት ቦክሰኞች፤ በ48፣ 52፣ 57፣ 63፣ 69፣ 75 እና 81 ኪሎ ግራም ተወዳዳሪ ሆነው ነበር፡፡ ከዳካር የአየር ጸባይ ጋር ለመለማመድ እንዲያስችላቸውም መቀመጫቸውን በአርባ ምንጭ በማድረግ ለረጅም ጊዜ በልምምድ ላይ መቆየታቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥቂቱ መነቃቃት የታየበት የቦክስ ስፖርት በአህጉር አቀፍ ውድድሮች ላይ ሜዳሊያዎችን ማስቆጠርና ተወዳዳሪነቱን በማስመስከር ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም ትናንት ወደ ሃገሩ የተመለሰው ብሄራዊ ቡድኑ በማጣሪያው የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ቶኪዮ ያቀናል የሚል ከፍተኛ ግምትም አግኝቶ ነበር፡፡ በሴኔጋል በነበራቸው ቆይታም የመጀመሪያዎቹን ዙሮች በብቃት በማለፍ ያላቸውን ተስፋ ማሳየት ችለዋል፡፡ ዙሩ እየገፋና እየከበደ መሄዱን ተከትሎም ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ ይሁን እንጂ ሶስት ቦክሰኞች እስከ ስምንት ባለው ደረጃ በመግባት ጥቂት ትኩረት ቢያገኙ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ ማረጋገጣቸውን በኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን የውድድር ስልጠና ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ስንታየሁ ተስፋዬ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ገልጸዋል፡፡ በአልጀሪያ በተካሄደው የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክ እንዲሁም በሞሮኮ ራባት የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤት የነበረው የ48 ኪሎ ግራም ተወዳዳሪው ዳዊት በቀለ ስምንት ውስጥ ከገቡት መካከል አንዱ ነው፡፡ የ57 ኪሎ ግራም ተወዳዳሪው ፍቅረማሪያም ያደሳ እና በ81 ኪሎ ግራም ተወዳዳሪው ሰይፈ ከበደም ስምንት ውስጥ መግባት የቻሉ ቦክሰኞች ናቸው፡፡ ቡድኑ ባይሳካለትም ወደ ሴኔጋል ያቀናው በኦሊምፒኩ ተካፋይ ለመሆን የሚያስቻለውን ውጤት ለማስመዝገብ ካልተቻለ ደግሞ እስከ አራት ያለውን ደረጃ ለመያዝ ነበር፡፡ ነገር ግን የትኩረትና የልምድ ማነስ እንዲሁም በልምምድ ወቅት ባጋጠመው የቁሳቁስ እጥረት ወደ ታላቁ የስፖርት መድረክ ማለፍ ሳይቻል መቅረቱን ባለሙያው ይጠቁማሉ፡፡ ከዚህ ባሻገር ዳኝነት ላይም መስራት እንደሚገባም ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ አዲስ ዘመን የካቲት 23/2012  ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=28199
[ { "passage": "ከቀናት በፊት የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና የዓለም አትሌቲክስ ከአስር ወራት ያነሰ ጊዜ የቀሩትን የቶኪዮ ኦሊምፒክ የማራቶንና እርምጃ ውድድሮችን የሚካሄዱበትን ስፍራ ከዋና ከተማዋ ቶኪዮ ለመሰረዝ ሃሳብ አቅርበው ነበር፡፡ ከፍተኛ ሙቀት አትሌቶቹን ሊጎዳቸው እንደሚችል በማሰብ የተነሳው ይህ የስፍራ ለውጥ ሃሳብም በአዘጋጇ ጃፓን ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘ አይመስልም። በቅርቡ በተካሄደው 17ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በኳታር የነበረው የአየር ሁኔታ በተለይ ለማራቶን ስፖርት አስቸጋሪ እንደነበር ይታወሳል። በአየር ሁኔታው ሳቢያ ባልተለመደ መልኩ ውድድሩ በእኩለ ሌሊት እንዲደረግ ቢወሰንም በተለይ በሴቶች በኩል ከተሳተፉት 68 አትሌቶች 28 የሚሆኑት ውድድሩን ማቋረጣቸው እንዲሁም ለጤና መታወክ መዳረጋቸውም አይዘነጋም። ይህም ስፖርቱን በሚመሩት ዓለም አቀፍ አካላት ዘንድ ስጋት ያሳደረ ሲሆን፤ እአአ የ2020ው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በሚካሄድበት ወቅት የሚኖረው የሙቀት መጠን ለጎዳና ላይ ውድድሮች ምቹ እንደማይሆን ተገንዝበዋል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲሁም የዓለም አትሌቲክስ በባለሙያዎቻቸው አማካኝነት ባደረጉት ጥናት በሐምሌ ወር በቶኪዮ የሚኖረው ሙቀት ከፍ እንደሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል፡፡ ይህም ለማራቶን እና እርምጃ ተወዳዳሪዎች ጤና እክል ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል። በመሆኑም እነዚህ ውድድሮች ከዋና ከተማዋ ቶኪዮ ነፋሻማ አየር ወዳለው ሰሜናዊው የሃገሪቷ ክፍል የማዘዋወር ሃሳብ አቅርበዋል። የውድድር ስፍራውን የለውጥ ሃሳብም ዓለም አቀፎቹን ማህበራት የውድድሩን አዘጋጅ ኮሚቴ እንዲሁም የሚመለከታቸውን አካላት ለማወያየት በተያዘው ወር መጨረሻ ለመገናኘት ቀን ቆርጠው ነበር። ኤኤፍፒ የሃገሪቷን መገናኛ ብዙሃን ዋቢ አድርጎ ባስነበበው ዘገባ መሰረት የውድድሩ አዘጋጆች በዚህ ሃሳብ ደስተኛ አይመስሉም፤ ይልቁንም የውድድር ማስጀመሪያ ሰዓቱ ላይ ለውጥ ማድረግ እንደሚሻል አመላክተዋል። ከመንግስታዊ አካል የተወከሉት ዩሪኮ ኮኬ «በውድድር ስፍራው መለወጥ ሃሳብ አልስማማም» ያሉ ሲሆን፤ መንግስት ዓለም አቀፎቹ ተቋማት ካነሱት ተቃራኒ ሃሳብ በመያዝ ውይይቱ ላይ እንደሚቀርብ ገልጸዋል።ለዚህ እንደ ምክንያት የተነሳውም የለውጡን ሃሳብ ኦሊምፒክ ኮሚቴው በድንገት ማንሳቱን ተከትሎ የሳፖሮ ከተማ ከንቲባዎች ምንም ዓይነት ዝግጅት ያላደረጉ በመሆናቸው ነው። ከዚህም ባሻገር የኦሊምፒኩ አዘጋጆች የማራቶን እና እርምጃ ውድድር በሚካሄድባቸው ስፍራዎች የሙቀት መጠኑን ሊቀንሱ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎችን እንደሚጠቀሙም ጠቁመዋል። ውድድሩን ለመመልከት ለሚፈልጉ የስፖርቱ ወዳጆች ትኬት የተቆረጠ መሆኑ ደግሞ ሌላ ቀውስ ሊያስከትልባቸው የሚችል መሆኑ አዘጋጆቹን አሳስቧቸዋል። ተወካዩ አክለውም «በርካታ የቶኪዮ ነዋሪዎች ስለ ውድድር ስፍራው ለውጥ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጥያቄ አቅርበዋል። የሃሳቡ አቀራረብም ለመንግስት አካላት እንዲሁም ለስፖርቱ ቤተሰብ ያልታሰበና ድንገተኛም ነው» ብለዋል። አዘጋጆቹ በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው የጠየቁም ሲሆን፤ ከኮሚቴው የውድድር አስተባባሪ ኮሚሽን ሊቀመንበር ጆን ኮቴስ ጋር ለመነጋገር ማቀዳቸውንም ዘገባው ተመልክቶታል፡፡ ውድድሩን የሚመሩት\nዓለም አቀፍ\nተቋማት ሙቀቱ\nበአትሌቶች እንዲሁም\nበውድድሩ ላይ\nተጽእኖ ማሳደሩ\nእንደማይቀርና በቅድሚያ\nየሚያሳስባቸው የአትሌቶች\nደህንነት መሆኑን\nአስታውቀዋል። ይሁን\nእንጂ ሃሳቡ\nየቀረበው የዓለም\nቻምፒዮናውን መካሄድ\nተከትሎ እንዲሁም\nውድድሩ ሊካሄድ\nዘጠኝ ወራት\nብቻ ሲቀሩት\nነው። ኦሊምፒክ ኮሚቴው ለውድድሮቹ ማካሄጃ ምቹ ይሆናል በሚል የመረጡት፤ ከቶኪዮ በ800ኪሎ ሜትር ርቀት በሆካኢዶ ተራራማ አካባቢዎች የሚገኘውን ሳፖሮ የተባለ ስፍራ ነው። በሰሜናዊው የሃገሪቷ ክፍል የሚገኘው ይህ ስፍራ ውድድሩ በሚካሄድበት ወቅት የአየር ሁኔታው በተሻለ መጠን የሚቀዘቅዝ መሆኑ አትሌቶችን እንደሚረዳቸው ይታሰባል። ስፍራው እአአ 1972 የክረምት ኦሊምፒክ የተካሄደበትም እንደነበር ይታወሳል።አዲስ ዘመን ጥቅምት 15/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "75b134abed3dd6d1797ec574bda2a2ad" }, { "passage": "ድልን ለማብሰር ከማራቶን እስከ አቴንስ የሮጠው ግሪካዊው መልዕክተኛ ፊሊፒደስ፣ በባዶ እግሩ 42 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ለጥቁሮች ኩራት ለዓለም ህዝብ ትንግርት የሆነው አበበ ቢቂላ፣ ለጥቁሮች መብት ትግል ከኦሊምፒክ ስኬት ይልቅ ሰብዓዊነትን ያስቀደመው ቦክሰኛው መሃመድ አሊ፣ በቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት በእንብርክክ ተማጽኖው የአምስት ዓመታትን የእርስ በእርስ ግጭት ማብቂያ ያበጀለት የእግር ኳስ ፈርጥ ዲድየር ድሮግባ፣… ዓለም ካከበራቸው ታሪክም ከጀግኖች መዛግብት ካሰፈራቸው ስፖርተኞች ጥቂቶች ናቸው። ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ወዲህ ስፖርት በሰው ልጅ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ውስጥ ሰፊውን ድርሻ መያዙ ገሃድ ነው። በዚህ ተወዳጅ ክንዋኔ ላይም በጦርነት አውድ ከሚዋደቁት ባላነሰ በርካታ ጀግኖች ተፈጥረው አልፈዋል፤ በዚህ ዘመንም እየተፈጠሩ ይገኛሉ። ስፖርተኞች ደረታቸውን ለጥይት ነፍሳቸውንም ለአገራቸው መገበር ባይጠበቅባቸውም፤ በእልህ አስጨራሽ ትግል ነጭ ላባቸውን አፍስሰው በሚያገኙት ድል ግን አገራቸውን ያስጠራሉ፣ ባንዲራቸውንም በማውለብለብ ህዝባቸውን ያኮራሉ። ታሪክም ከራሳቸው ይልቅ ህዝባቸውን ያስቀደሙ፤ ራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠውም አገራቸውን ያስጠሩትን እነዚህን ጀግኖች እያነሳ ሲዘክራቸው ይኖራል። ለዛሬም ከጀግና ስፖርተኞች መካከል አንዱን 100 ዓመታትን ወደኋላ ተመልሰን እናስታውስ። በአገረ አሜሪካ ከታዩ ስፖርተኞች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል፤ ጂም ትሮፔ። በኦሊምፒክ ተሳትፎው ያሳየው ቁርጠኝነት አገር ወዳድነቱን የመሰከረ ሲሆን፤ ተግባሩም ለብዙዎችም ትምህርት ሆኗል። እርግጡን የሚያወሳ የልደት የምስክር ወረቀት ባይገኝም አሁን ኦክለሃማ ከተሰኘው የአሜሪካ ግዛት እ.አ.አ በ1887 እንደተወለደ በህይወት ታሪኩ ተጠቅሷል። ትሮፔ በልጅነቱ ከባድ እና ውስብስብ የሆነ ቤተሰባዊ ህይወት የነበረው ሲሆን፤ የመንትያ ወንድሙ እናቱ እንዲሁም የአባቱ ሞት ደግሞ የልጅነት ህይወቱን ይበልጥ ፈታኝ ሊያደርግበት ችሏል። ትምህርቱን ለበርካታ ጊዜ እያቋረጠ እና እየቀጠለ ቢቆይም፤ ፔንሲልቫኒያ በሚገኝ የኢንዱስትሪ ትምህርት ቤት ተማሪ በነበረበት ወቅት ስፖርታዊ ተሳትፎውን ጀምሯል። እንደ እድል ሆኖም በወቅቱ በአሜሪካ ስመጥር በሆኑት የእግር ኳስ አሰልጣኝ ግሌን ስኮቤይ የመሰልጠን አጋጣሚ ተፈጥሮለት ነበር። ነገር ግን በዚያው ዓመት አሰልጣኙ ከዚህ ዓለም በማለፋቸው ከስፖርት ሊርቅ የግድ ሆነበት፤ ከዓመታት በኋላ ኮሌጅ እስኪገባ ድረስም በድጋሚ ወደ ስፖርት አልተመለሰም ነበር። ወደ ስፖርት ከተመለሰ በኋላም በእግር ኳስ እና ቤዝቦል ስፖርቶች ባሻገር በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች መሳተፍ ብቃቱ ተደናቂ አድርጎት ቆይቷል። ከኮሌጅ ቡድን እስከ ክለቦች ድረስም በተለያዩ ውድድሮች ላይ ተሳትፎ ሻምፒዮን ለመሆን ችሏል። በእግር ኳስ ስፖርት የነበረው ብቃት በተለይ የሚደነቅ ይሆን እንጂ በአትሌቲክስ ስፖርቶች ላይ የሚያሳየው ችሎታ ግን የሚያስገርም ነበር። ይህንን ተከትሎም እ.አ.አ በ1912 የስዊድኗ ስቶኮልም አዘጋጅ ለሆነችበት ኦሊምፒክ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድንን ከሚወክሉት መካከል አንዱ በመሆን ተመረጠ። ወቅቱ የፔንታቶሎን እና ዴክታቶሎን የውድድር ዓይነቶች በኦሊምፒክ የተካተቱበት እንደመሆኑም ቶርፔ የታጨው ለእነዚህ የውድድር ዓይነቶች ነበር። የውድድሩ ዕለት ደርሶም ቶርፔ አስደማሚ ብቃቱን ለዓለም ሊያሳይ ሰዓታት ብቻ ቀሩት። ነገር ግን የእዚያን ዕለት ጠዋት ከእንቅልፉ ሲነቃ ጫማውን ካስቀመጠበት ሊያገኝ አልቻለም፤ ከፍለጋ በኋላም እንደተሰረቀ አወቀ። በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ መሳተፍ በግሉ ከሚያስገኝለት ክብር በላይ አገሩን መወከል የዜግነት ግዴታው በመሆኑ ተስፋ መቁረጥ የማይታሰብ ነው። በመሆኑም በአጋጣሚው ከመቆጨት ይልቅ አማራጭ ፍለጋውን ተያያዘው። ከቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቅርጫት ውስጥም አገልግሎት የማይሰጡ ሁለት የተለያዩ ጫማዎችን አገኘ። የውድድር ሰዓቱ እየደረሰ በመሆኑም ጫማዎቹን ሳያቅማማ ለካቸው። አንዱ ጫማ ለእርሱ የማይሆን ሰፊ መሆኑ ሌላ ችግር ነበር። ምን ማድረግ እንዳለበትም አሰበ፤ ያገኘው መላም ሰፊውን ጫማ በሁለት ካልሲዎች ደራርቦ ማድረግ ነበር፤ እናም አደረገው። የእርሱ ባልሆኑት ሁለት ዓይነት ጫማዎችን በነጭ እና ጥቁር ካልሲዎች ተጫምቶም ወደ ውድድር ስፍራው አመራ። በተሳተፈባቸው ሁለት ውድድሮችም ብቃቱን አስመሰከረ። ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለማጥለቅ በቃ። በፔንታቶሎን (ርዝመት ዝላይ፣ ዲስከስ ውርወራ፣ አጭር ርቀት ሩጫ እንዲሁም ትግል) ካደረጋቸው አምስት ውድድሮች መካከል አንዱን ብቻ ተሸንፎ (በጦር ውርወራ) በሰበሰባቸው ነጥቦች ብልጫ አሸናፊ ሊሆን ችሏል። በተሳተፈባቸው የፔንታቶሎን እና ዴክታቶሎን 15 ውድድሮች በድምሩ ስምንቱን በማሸነፍም የቁጥር አንድነትን ማዕረግ ለመጎናጸፍ ችሏል። ቶርፔ በወቅቱ በውድድር አሸናፊነቱ ካጠለቃቸው ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎች ባሻገር ሌሎች ሁለት ሽልማቶችንም ተቀዳጅቷል። የመጀመሪያው ገጸ- በረከት\nበውድድር አዘጋጇ አገር ስዊድን ንጉስ ጉስታቭ አምስተኛ እጅ የተበረከተለት ሲሆን፤ «የዓለም ምርጡ አትሌት ነህ» በማለትም አበረታተውታል። የሩሲያው ኒኮላስ ሁለተኛም ለትሮፔ ሁለተኛውን የማበረታቻ ሽልማት ሰጥተውታል። ነገር ግን ይህ ታሪክ በጋዜጦች ታትሞ ለንባብ የበቃው ትሮፔ ገድሉን ከፈጸመ ከ36 ዓመታት\nበኃላ እ.አ.አ በ1948 ነበር።\nመጽሐፍትም በስሙ ተጽፈው ገበያ ላይ የዋሉት እ.አ.አ በ1952 ነው።\nአትሌቱ ከዓመታት በኋላ በዓለም ላይ ታዋቂ መሆኑ በአሜሪካ ዜጎች ልብ ሰፊ ቦታ አላሳጣውም፤ አሁንም ድረስ ብዙዎች «ጀግናችን» ሲሉ ያወድሱታል። በፔንሲልቫኒያ ግዛትም በስሙ «ጂም ቶሮፔ» በሚል የተሰየመ ከተማ አለው።አዲስ\nዘመን ሚያዚያ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "18c14ba7775635036928a87643636857" }, { "passage": "እአአ የ1964ቱ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያ በታሪኳ ተሳታፊ የሆነችበት ሶስተኛው ኦሊምፒክ ነው። ታላቁ አትሌት አበበ ቢቂላ በኦሊምፒክ ማራቶን ለራሱ እና ለአገሩ ሁለተኛውን፣ በውድድሩ ደግሞ ብቸኛውን ሜዳሊያ ያገኘበትም ነበር። አሁን ደግሞ ጃፓን ከሃምሳ ስድስት ዓመታት በኋላ ኦሊምፒክን በምድሯ ለማስተናገድ ወራት ብቻ የቀሩበት ጊዜ ላይ እንገኛለን። በዚህ ታላቅ የስፖርት መድረክም የተሻለ ታሪክ ለማስመዝገብ ኢትዮጵያ በተለየ ትኩረት በመንቀሳቀስ ላይ ትገኛለች። በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ ከውጤታማነት ባሻገር ተሳትፎም ክብርን ያስገኛል። በውጤታማነት ድርብ ክብርን ለመጎናጸፍ ደግሞ ትኩረት፣ ጥረትና ጽናት አስፈላጊ መሆናቸው ይታመናል።በኦሊምፒክ መድረክ የአገሪቷን ስም በተደጋጋሚ ያስጠራው እንዲሁም ከፍተኛውን የውጤታማነት\nስፍራ የሚይዘው የአትሌቲክስ ስፖርት ነው። ኢትዮጵያ ደግሞ በዚህ ስፖርት በተመዘገቡ ሜዳሊያዎች አማካኝነት ከውጤታማዎቹ አገራት\nመካከል 36ኛ ስፍራ ላይ ትገኛለች። ነገር ግን በዚህ መድረክ ውጤታማ ያደረጓት አትሌቶች የኋላ ታሪክ ቢጠና በግላቸው የሚያደርጉት\nጥረትና ጽናት ሰፊውን ድርሻ ይይዛል። በመሆኑም መንግስት የተሻለ ትኩረት በመስጠት ውጤታማነቱን ለማሳደግና ለማገዝ እየተንቀሳቀሰ\nመሆኑን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አስታውቋል። ለዚህም የመጀመሪያው ርምጃ አትሌቶች የዝግጅት ጊዜያቸውን በትኩረት እንዲያሳልፉ በተሻለ\nስፍራ እንዲያርፉ ማድረግ ነው። በመሆኑም የዝግጅት ኮሚቴው ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጋር ባደረጉት ውይይት\nለውድድሩ የተመረጡ አትሌቶች ካምፓቸውን ከፍተኛ ደረጃ ካላቸው ሆቴሎች መካከል በአንዱ እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተሰጥቷል። በዚህም መሰረት\nበኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጥሪ የተደረገላቸው አትሌቶች ተሰባስበው ወደ ልምምድ እንደሚገቡ ተገልጿል። ከዚህ ቀደም በብሄራዊ\nቡድን የታቀፉ አትሌቶች የላብ መተኪያ ወጪ እጅግ አናሳ መሆኑ በቅሬታ መልክ የሚነሳ ነበር። ይህንንም ለመቅረፍ በመንግስት በኩል\nበተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ለታዋቂ አትሌቶች 50ሺ ብር ደሞዝ እንዲያገኙ እንዲሁም ለሌሎች ጀማሪ አትሌቶች 10ሺ ብር በየወሩ የሚከፈላቸው\nይሆናል። በልምምድ ግብዓት እንዲሁም ትጥቅ በኩልም ችግር እንዳይገጥማቸው እየተሰራ መሆኑም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከአትሌቲክስ\nፌዴሬሽን ጋር በመሆን ከትናንት በስቲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጧል። ዝግጅቱን በበላይነት\nየሚመራው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከስፖርት ማህበራትና ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በመሆን ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ዝግጅ በማድረግ ላይ\nእንደሚገኝ ይታወቃል። ለዝግጅቱም የቶኪዮ ብሄራዊ ዝግጅት ኮሚቴ እንዲሁም የቶኪዮ ኦሊምፒክ ቴክኒክ ኮሚቴ በሚልም ሁለት ኮሚቴዎችን\nአዋቅሯል። ብሄራዊ ኮሚቴው በቀድሞ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ የሚመራ ሲሆን፣ ትኩረቱን በሃብት አሰባሰብ፣\nየልማት ስራዎች፣ የደጋፊ አባላት ላይ እንዲሁም በስፖርተኞች ሽኝትና አቀባበል ላይ ያደርጋል። በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል\nኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጂሎ የሚመራው የቴክኒክ ኮሚቴው ደግሞ ከተለያዩ ባለሙያዎች ጋር በመሆን በአትሌቶችና አሰልጣኞቻቸው ምርጫ ላይ\nየሚሰራ ይሆናል። በዚህም መሰረት\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እጩ አትሌቶችንና አሰልጣኞቻቸውን ከቀናት በፊት አሳውቋል። በማጣሪያ ውድድር ላይ ያሉት የቦክስና ወርልድ ቴኳንዶ\nስፖርቶችን ጨምሮ ከውሃ ስፖርቶችና ብስክሌት ፌዴሬሽኖችም ጋር ኮሚቴው በትብብር በመስራት ላይ ይገኛል። ቀደም ብሎ ወደ ዝግጅት\nምዕራፍ በመግባት ላይ የሚገኘው የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በበኩሉ 90 አትሌቶችንና 15 አሰልጣኞችን በማጨት ወደ ልምምድ ለመግባት\nበመንደርደር ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል። ብሄራዊ ቡድኑ በሶስት ምዕራፍ የተከፈለ ዝግጅት የሚያደርግ ሲሆን፤ በመጨረሻም 50 አትሌቶች\nወደ ቶኪዮ የሚጓዙ ይሆናል። ለጊዜው በተሳትፎ ደረጃ የተያዘው ከ800ሜትር እስከ እርምጃ ባሉት ርቀቶች ቢሆንም ሚኒማውን ማሟላት\nከተቻለ በ400ሜትርም ተሳታፊ የመሆን እድል እንደሚኖር ተጠቁሟል።የቴክኒክ ኮሚቴው\nቀድሞ ዝርዝራቸው ይፋ የተደረጉትን አሰልጣኞች የተመረጡበት መስፈርትም በርካታ አትሌቶችን በማስመረጥ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ውድድሮች\nባላቸው ልምድ መሆኑን ገልጿል። የአትሌቶች የምርጫ መስፈርት ደግሞ እአአ በ2019 ባስመዘገቡት ሰዓት መሰረት በመምረጥ በስራ አስፈጻሚ\nኮሚቴው የጸደቀ መሆኑ ተብራርቷል። ለኦሊምፒክ የሚደረገው\nዝግጅት አገርን ለማስጠራት የሚደረግ እንደመሆኑ በሁሉም አካላት ዘንድ በተለይም በአትሌቲክስ ፌዴሬሽንና ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች\nበኩል ያለው አለመግባባትን ከወደ ጎን በመተው ለውጤታማነት በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑ በመግለጫው ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን አርብ የካቲት 13/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "b91076268f89ce5d1de2ac6ab4f9b259" }, { "passage": "የዘንድሮው ዓመት የአትሌቲክስ አፍቃሪዎች ከዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ማግስት የታላቁን ስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ መዳረሻ በጉጉት የሚጠብቁበት በመሆኑ በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ የሚናፈቅ ነበር። የስፖርት ማህበራት የማጣሪያ ውድድሮችን በማካሄድ አገራትም ብሄራዊ ቡድኖቻቸውን በመመልመል ወደ ዝግጅት በመግባት ላይ እንደነበሩም ይታወሳል። ነገር ግን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ የዓለም ህዝብ ስጋት በመሆኑ ምክንያት ታላቁ ኦሊምፒክ ሊራዘም ችሏል። ከኦሊምፒኩ ጎን ለጎንም የበጋውን መግባት ተከትሎ በርካታ የግልና ዓለም አቀፍ ውድድሮችም የሚካሄዱበት ወቅት ቢሆንም በርካቶች በተመሳሳይ ምክንያት ተሰርዘዋል። \nኦሊምፒኩ ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሟል ይባል እንጂ ከሰሞኑ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ከዚያም በላይ ለሆነ ጊዜ ሊቆይ እንደሚችልና ከነጭራሹ የመሰረዝ እድል ሊገጥመው እንደሚችል ይጠቁማሉ። ምክንያቱ ደግሞ በመቶ ሺዎች የሚቆሩ ሰዎችን እየገደለ ያለው ወረርሽኝ ክትባት አሊያም መድሃኒት የሚያገኝለት የሕክምናው ዓለም ጠበብት እስካሁን ባለመኖሩ ነው። ይህም ለረጅም ጊዜ የተዘጋጁ አትሌቶችን ልፋት ገደል መክተቱ ሳይበቃ ተስፋ ለመቁረጥና ልምምድ ለማቆም እንዳያስገድዳቸው አስጊ ሆኗል። በአትሌቲክስ ስፖርት ውጤታማ በሆነችው ኢትዮጵያ በርካታ አትሌቶች የዚህ ችግር ተጋላጭ ሊሆኑ እንደሚችል ይገመታል። ያም ሆኖ አትሌቶች ይህን ክፉ ጊዜ በብልሃት ማለፍ እንዳለባቸው ይታመናል። \nበቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን ለመወከል ተመርጠው የነበሩ አትሌቶች በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ያሉበት ሁኔታ ምን ይመስላል፣ መራዘሙ ምን አስከተለባቸው፣ አትሌቶችና አሰልጣኞችስ ይህ ወቅት እስኪያልፍ ምን እያከናወኑ ይቆያሉ በሚሉ ጉዳዮች ላይ አዲስ ዘመን የበሄራዊ ቡድኑን አባላት አነጋግሯል። \nየቶኪዮ ኦሊምፒክ ተሳታፊ የሆኑ አትሌቶችና አሰልጣኞች ተመርጠው ወደ ሆቴል እንዲገቡ በማድረግ ሂደት ላይ ሳለ የመራዘሙ ዜና መሰማቱን የሚገልጹት የብሄራዊ ቡድኑ አስተባባሪና የረጅም ርቀት ዋና አሰልጣኝ ሱፐር ኢንቴንደንት ሁሴን ሸቦ ናቸው። መንግስት ባወጣው አቅጣጫ መሰረትም\n የቡድኑ አባላት በየቤታቸው ተበትነው እንዲቆዩ ተወስኗል። ይሁን እንጂ አትሌቶች በያሉበት ቦታ ሆነው በሳምንት ለአምስት ቀናት በግላቸው ቀላል እንቅስቃሴዎችን እንዲሰሩ እየተደረገ ነው። ቀድሞ ከሚሰሩት ለሁለት ቀናት እያረፉ 80 በመቶ የሚሆንና አቋምን ጠብቆ ለማቆየት የሚሰሩ እንቅስቃሴዎች ላይ እንዲያተኩሩ አሰልጣኞች አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ይህንንም አሰልጣኞችና አትሌቶች ቴሌግራምን በመሰለ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እንዲሁም በስልክ እየተወያዩ ተግባራዊ እንደሚያደርጉም አሰልጣኙ ይጠቁማሉ። \nየረጅም ርቀት ሩጫዎች ከትንፋሽ ጋር የተያያዘ እንደመሆኑ ከስልጠናው ጎን ለጎን በተለየ መልኩ የሚታይ ነው። በመሆኑም አትሌቶች ከሌላው ህብረተሰብ በተለየ ከ2 እስከ 5 ሜትር የሚሆን መጠን ርቀታቸውን መጠበቅ እንዳለባቸው ይታመናል። ከዚህ ባሻገር የመተጣጠፍ፣ የጂምናስቲክና ሌሎች የማሳሳቢያ እንቅስቃሴዎችን በሚያከናውኑበት ወቅትም የተስተካከለ የአየር ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጥ እንዳለባቸው የሚጠቁሙት ዋና አሰልጣኙ ናቸው። ከአካል ብቃቱ ባሻገር በአእምሮም ብቁ እንዲሆኑና እንዳይረበሹም አሰልጣኞች ያስገነዝባሉ።\nየውድድሩ መራዘም በአትሌቶች ዘንድ ምን ተፅዕኖ እንዳሳደረ የብሄራዊ ቡድኑ አባልና ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ተሞክሮውን ያጋራል። ኦሊምፒክ በአራት ዓመት አንዴ የሚመጣ ውድድር\n እንደመሆኑ ለአትሌቶች ትልቅ እድል የሚፈጥርና በጉጉት የሚጠበቅ ነው። በመሆኑም አትሌቶች እድሉን በመልካም ለመጠቀም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ እንደነበሩም ያስታውሳል። እርሱም ከግል አሰልጣኙ ጋር በመሆን ከአንድ ዓመት በፊት እቅድ በማውጣት ልምምድ የጀመረ ሲሆን፤ በጃፓን ጥሩ ውጤት የማስመዝገብ እቅድ ነበረው። የኦሊምፒኩ መራዘም እስኪሰማ ድረስም በመልካም ዝግጅት ላይ ቆይቷል። \nብሄራዊ ቡድኑ ከተበተነ በኋላም በግሉ ከውድድር ውጪ የሚሰሩ እንቅስቃሴዎችን ከማድረግ ወደኋላ አለማለቱን በዶሃ የዓለም ቻምፒዮና የ5 ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊው አትሌት ሰለሞን ይጠቁማል። ስልጠናውም ቀድሞ ከሚሸፍነው ርቀት ያነሰ የትንፋሽ፣ ጂምናስቲክና ሌሎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን እንደሚያጠቃልል ይናገራል። ይህንንም ከታናሽ ወንድሙ ጋር በመሆን ርቀታቸውን በጠበቀ መልኩ በቤትና ወደ ጫካ በመሄድ ያከናውናሉ። ከአሰልጣኞችም አትሌቶች በብቃታቸው እንዲቆዩ ለማድረግ በስልክና በሌሎች መንገዶች ግንኙነታቸውን እንደቀጠሉ ያብራራል። \nየኦሊምፒኩ መራዘም በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ በአዘጋጇ ጃፓን፣ በተሳታፊ አገራት እንዲሁም አትሌቶች ዘንድ ተጽእኖ ማሳደሩ ይታወቃል። በአንጻሩ የጠቀማቸውም አልጠፉም፤ እነርሱም በጉዳት ምክንያት ለኦሊምፒኩ ብቁ\n ያልነበሩ አትሌቶችን መሆናቸውን አሰልጣኝ ሁሴን ይጠቁማሉ። ከዚህ ባሻገር ወጣትና ተተኪ አትሌቶችን ለአንድና ከዚያ በላይ ላለ ዓመት መራዘሙ የሚጠቅማቸውና ወደ ተወዳዳሪነት እንዲመጡ እድል የሚሰጥ እንደሚሆንም እምነት አላቸው። ምናልባትም ስጋት ሊሆን የሚችለው በጥሩ ብቃት ላይ ለሚገኙ ኤሊት አትሌቶች ሲሆን፤ ምክንያቱ ደግሞ በአንድ ዓመት ልዩነት ሊከሰት የሚችለውን የአቋም መውረድ ወይም ጉዳት ማስተናገድ ለመገመት አዳጋች በመሆኑ ነው። በጥቅሉ ሲታይም መዋዕለ ነዋይ ላፈሰሱ አገራትና በእቅድ ሲንቀሳቀሱ ለቆዩ አሰልጣኞችና ስፖርተኞች እንዲሁም ሌሎች አካላት ጉዳቱ በቀላሉ የሚገመት እንዳልሆነ ያስቀምጣሉ። በመሆኑም ይህ ለዓለም ስፖርት ከፍተኛ ኪሳራ የሚያስከትል መሆኑን ይናገራሉ። \nበኦሊምፒክ ለትልቅ ውጤት ከሚጠበቁት አትሌቶች መካከል አንዱ የሆነው ሰለሞንና ሌሎች የቡድን አጋሮቹ በጥሩ አቋም ላይ እያሉ ውድድሩ በመራዘሙ ደስተኛ እንዳልሆነ ወጣቱ አትሌት ይናገራል። ምክንያቱ ደግሞ አሁን ያለበትን ብቃት በቀጣዩ ዓመት ላያገኘው ስለሚችል ነው። ነገር ግን ቀዳሚው የሰው ልጅ ህይወት በመሆኑ ደስተኛም ባይሆን ከሁኔታዎች ጋር ራሱን ለማስማማት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ሌሎች አትሌቶችም ከክለብ የተበተኑ በመሆኑ በተለያዩ ስፍራዎች ይገኛሉ። በዚህ ምክንያትም ልምምድ ከማቋረጥ ይልቅ ከአቋማቸው እንዳይወርዱ ጥንቃቄ እያደረጉ ባሉበት ሆነው ዝግጅታቸውን ቢቀጥሉ መልካም እንደሆነ ምክረሃሳቡን ያጋራል። በክፍለ አገር የሚገኙ ባልደረቦቹም የሚያገኙትን መረጃ ለሌሎችም እንዲያጋሩ መክሯል። \nአሰልጣኙ በበኩላቸው ለአትሌቶች ‹‹ከህይወት በላይ ምንም የለም፤ የትኛውም ነገር ይደረስበታል። በመሆኑም መንግስትና የጤና ሚኒስትር የሚያወጧቸውን መመሪያዎችና አቅጣጫዎች መከተል አስፈላጊ መሆኑን ያስታውሳሉ። እጅን መታጠብ፣ ርቀትን መጠበቅ፣ በሰዎች መካከል ሲገኙ አፍና አፍንጫን መሸፈን እና የህመም ምልክቶች ሲሰሟቸው ለጤና ባለሙያዎች በፍጥነት ማሳወቅ አለባቸው›› ሲሉም ያስገነዝባሉ። ከአትሌቶች ወጪ ያሉ ዜጎችም ይህ ወቅት እስኪያልፍ ግንኙነታቸውን ከቀድሞው እንዲቀንሱና በመንግስት የተቀመጠውን አቅጣጫ ያለመወላወል ተግባራዊ እንዲያደርጉም ጥሪያቸውን ያቀርባሉ።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 26/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "27dde6a31e62972ae266112506eedf87" }, { "passage": "የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ ከሰጣቸው ታላላቅ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች አንዱ የሆነው የፎኮካ ማራቶን ከሳምንት በኋላ በጃፓን ይካሄዳል፡፡ በዚህ ውድድር የሚፎካከሩ የዓለማችን ጠንካራ አትሌቶች ስም ከወዲሁ ይፋ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን፤ የርቀቱ ኮከቦች የሆኑት ምሥራቅ አፍሪካውያን አትሌቶች የተለመደ የአሸናፊነት ግምት ተችሯቸዋል፡፡እኤአ በ2015 የቤጂንግ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በማራቶን ተከታትለው በመግባት የወርቅና የብር ሜዳሊያ ማጥለቅ የቻሉት ኤርትራዊው ግርማይ ገብረሥላሴና ኢትዮጵያዊው የማነ ፀጋዬ ትልቅ የአሸናፊነት ግምት ከተሰጣቸው አትሌቶች ግንባር ቀደም ናቸው፡፡ግርማይ ገብረሥላሴ በዓለም ቻምፒዮናው በአስራ ስምንት ዓመቱ ሳይጠበቅ ለታላቅ ድል በመብቃት ለኤርትራ በመድረኩ የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ ማጥለቁ የሚታወስ ሲሆን፤ በአንፃሩ በርቀቱ የተሻለ ልምድ የነበረው የማነ የብር ሜዳሊውን ለኢትዮጵያ ማስመዝገቡ አይዘነጋም፡፡ ሁለቱ የማራቶን ፈርጦች ከዓለም ቻምፒዮናው በኋላ በትልቅ ውድድር ዳግም ፎኮካ ማራቶን ላይ የሚያደርጉት ፉክክር የሚጠበቅ ይሆናል፡፡የማነ በበርካታ የማራቶን ውድድሮች በማሸነፍ ስማቸው ከሚጠቀስ የዓለማችን ድንቅ የማራቶን አትሌቶች አንዱ ሲሆን፤ ከሁለት ዓመት በፊት በዚሁ በፎኮካ ማራቶን 2:08:48 ሰዓት ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ይህም ሰዓቱ እኤአ 2012 ላይ በሮተርዳም ማራቶን ሲያሸንፍ ካስመዘገበው የራሱ ምርጥ ሰዓት በአራት ደቂቃ የተሻለ ሆኖ ተመዝግቦለታል፡፡ የማነ በዓለም ቻምፒዮናው የብር ሜዳሊያውን ካጠለቀ ወዲህ ጉልበቱ ላይ በገጠመው ጉዳት የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክን ጨምሮ በርካታ ውድድሮች ያመለጡት ሲሆን፤ ያለፈውንም ዓመት በጥሩ አቋም ላይ አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ በ2018 ወደ ጥሩ አቋም መመለሱን ባለፈው ሰኔ ወር የኦታዋ ማራቶንን 2:08:52 በሆነ ሰዓት በማሸነፍ አሳይቷል፡፡ግርማይ ገብረሥላሴ በበኩሉ ከዓለም ቻምፒዮናው ድሉ በኋላ በሪዮ ኦሊምፒክ ሌላ ታሪክ ይሠራል ተብሎ ሲጠበቅ ሜዳሊያ ውስጥ መግባት ሳይችል ቀርቷል፡፡ ይሁን እንጂ በዚህ ታላቅ መድረክ አራተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ እንደ ወጣት አትሌት መጥፎ የሚባል አልነበረም፡፡ከኦሊምፒኩ ስድስት ሳምንታት በኋላ በጠንካራው የኒውዮርክ ማራቶን ዳግም ሳይጠበቅ ለድል የበቃው ግርማይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ስሙን በርቀቱ ማግነን ችላል፡፡ 2:07:46 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያለው ግርማይ ባለፉት ሁለት ውድድሮቹ አቋርጦ መውጣቱ ምናልባትም ወደ ጥሩ አቋሙ ካልተመለሰ በዘንድሮው የፎኮካ ማራቶን ከየማነ ጋር የሚጠበቀውን ጠንካራ ፉክክር እንዳያሳይ ስጋት ሊሆን ይችላል፡፡በዚህ ውድድር የማነ ከግርማይ ባሻገር ከሌላ አትሌት ጠንካራ ፉክክር እንደሚገ ጥመው ይጠበቃል፡፡ ይህም ውድድሩ ላይ ከየማነ ቀጥሎ ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ይዞ የሚወዳደረው ኬንያዊው ቪንሰንት ኪፕሩቶ ሲሆን፤ በርቀቱ 2:05:13 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያለው አትሌት ነው፡፡\nበሌላ በኩል በዘንድሮው የፎኮካ ማራቶን ትኩረት ሳይሰጠው መታለፍ የሌለበት አትሌት ጃፓናዊው ዩኪ ካዉቺ ነው፡፡ ይህ አትሌት ካለፉት ዘጠኝ የፎኮካ ማራቶን ውድድሮች በስምንቱ ላይ በመሳተፍ ከሌሎቹ አትሌቶች የተሻለ ልምድ ማካበት ችሏል፡፡ ዩኪ ልምድ ማካበቱ ብቻ በውድድሩ አስፈሪ ወይንም ጠንካራ ተፎካካሪ ባያደርገውም በርቀቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያስመዘገበ ያለው ውጤትና ጥሩ አቀም ለምሥራቅ አፍሪካውያኑ አትሌቶች አስፈሪ ያደርገዋል፡፡ ዩኪ በዚህ ውድድር እኤአ በ2011፣2013እና 2016 ሦስተኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ በሦስቱም ውድድሮች ርቀቱን ከ2፡10 ሰዓት በታች በማጠናቀቅ ጥንካሬውን ማሳየት ችላል፡፡ ዩኪ ምሥራቅ አፍሪካውያን ደጋግመው ያሸነፉትን የቦስተን ማራቶን በቅርቡ ማሸነፉም በአገሩና በደጋፊዎቹ ፊት በሚያደርገው ውድድር ቀላል ግምት እንዳይሰጠው ያደርጋል፡፡", "passage_id": "ba0a2da0290d0ea00dd0d72866a0b83f" } ]
9814a087b269b74f41aae4af96a8ac14
ce05c9f4a505cf6c940856d39f7eba9a
የ6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ በተመራጭ ፎቶ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ እንደሚሆን ተገለፀ
ጽጌረዳ ጫንያለውአዲስ አበባ፡- ስድስተኛው አገር አቀፍ ምርጫ መራጭ የሚያውቀውን ሰው በትክክል አውቆ እንዲመርጥ በፎቶ የተደገፈ መረጃ እንደሚሰጠውና ሙሉ ምርጫው በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሁም የመረጃ ማስገቢያ ባለሙያ የተመደበበት ሆኖ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለፀ። ስድስተኛው አገራዋ ምርጫ ግንቦት 28 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚካሄድ በጊዜያዊነት ቀን ተይዞለታል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ላይ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በተወያየበት ወቅት እንደተገለፀው፤ ግንቦት 28 ቀን 2013 ዓ.ም እንዲካሄድ ጊዜያዊ የቀን ቀጠሮ የተያዘለት በስድስተኛው አገራዊ ምርጫ በርካታ አዳዲስ አሠራሮችና ቴክኖሎጂዎች ይተገበራሉ። ከእነዚህ መካከልም መራጭ ማንነቱንና ምንነቱን እየለየ እንዲመርጠው የሚያስችል ተመራጭ እንዲኖረው ለማድረግ በፎቶ የተደገፈ ምርጫ መሆኑ ተጠቃሽ ሲሆን፤ ሌላው በባለሙያ የተደገፈ መረጃ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ላይ እንዲኖር ለማድረግ የመረጃ ማስገቢያ ባለሙያ ለምርጫው ዝግጁ መሆናቸው ነው። አጠቃላይ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ተግባሩ የዘንድሮው ምርጫ ለየት የሚያደርገው እንደሆነ የገለፀው ቦርዱ፤ ከምርጫ ምዝገባ እስከ ውጤት ድረስ ያሉ ተግባራት በቴክኖሎጂው አማካኝነት የሚከናወኑ እንደሆነም አስታውቋል። የምርጫ ምልክቶችም ቢሆኑ በሚገባ እንዲመረመሩ የሚያስችል አሠራር መዘርጋቱንም ጠቁሟል። ቦርዱ በዕለቱ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳን ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ ፊርማ ማሰባሰቡ ሂደት ላይ፤ የእጩ ምዝገባና ምርጫው የሚደረገው በኮቪድ ውስጥ ሆነን በመሆኑ የወረቀት ልውውጦችና የሰው ለሰው ግንኙነቶች በተቻለ መጠ ንግድ ያልሆኑትን መቀነስ ስለሚያስፈልግ እንዲሁ የፓርቲ ድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብ ላይ የታዩ ውስብስብ ሂደቶች በመኖራቸው ምክንያት በሕግ የተቀመጠውን ምርጫ ቦርድ መወሰን ስለማይችል ምክርቤቱ ምላሽ እንዲሰጥበት ማስገባታቸውን የገለፁት ደግሞ የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ናቸው። ወይዘሪት ብርቱካን እንደተናገሩት፤ ምርጫው በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን ከማድረግ ጎን ለጎን ለፖለቲካ ፓርቲዎች የተደላደለ ሜዳ የመፍጠሩ ግዴታ የቦርዱ ሃላፊነት ነው። መንግሥትም ከፖለቲካ ፓርቲዎች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት የመሥራት ግዴታውን መወጣት ይኖርበታል። ከዚህ ባለፈም ቀደም ሲል በነበሩ ምርጫዎች የተስተዋሉ የአሠራር ግድፈቶች እና ጫናዎች አሁን ላይ ቢሆን በታችኛው የመንግሥት መዋቅር አካባቢ በተወሰነ መልኩ የሚስተዋሉ በመሆኑ በዚህኛው ምርጫ እንዳይደገሙ ተገቢውን እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል።እንደብልጽግና ይህ ምርጫ የሚታየው በማሸነፍና በመሸነፍ ጠባብ ትርጉም ሳይሆን ታሪካዊ ክስተት በመፍጠር ታሪክ መሥራት እንዴት እንደምንችል አስበን እየተንቀሳቀስንበት ነው፣ ያሉት ደግሞ ገዢውን የብልጽግና ፓርቲን ወክለው በመድረኩ የተገኙት አቶ ዛዲግ አብርሃ በበኩላቸው፤ ታሪካዊ ምርጫ፣ ከተሸነፍን በሰላማዊ መንገድ ማስረከብ እንጂ እንደባለፈው የባከነ ዕድል እያሉ ከንፈር እየመጠጡ መቀጠል አንፈልግም ብለዋል። ካሸነፍን የበለጠ ብልጽግናን እናረጋግጣለን፤ ከተሸነፍን ደግሞ በታሪክ የሚጻፍ ሥራ ሠርተን ቦታውን ለተተኪው እንለቃለን። ምክንያቱም ይህ ምርጫ ለትውልዱ የሚሰጠውን ትርጉምም ስለምናውቅ ማጭበርበር ሳይሆን እውነተኛ ዴሞክራሲን በአገር ላይ ማሳየትም ዋና አላማችን ነው ሲሉም አብራርተዋል።ብልጽግና እንከን የለበትም፣ ንፁህ አባል ያለበት ነው ማለት አይቻልም የሚሉት አቶ ዛዲግ፤ የምርጫውን ሕግ የተላለፉ ሁሉ ቅጣታቸውን እንዲያገኙ እናደርጋለን ብለዋል። ከዚህ በፊትም የተለያዩ ስህተቶችን በማየታችን በሚገባ መፍትሄ ስንሰጥ ቆይተናል፤ ስለሆነም አሁንም አለ የተባለውን ነገር ከሥር መሠረቱ አጥንተንና አይተን መፍትሄ የምናስቀምጥ ይሆናል፤ ለዚህ ደግሞ መጀመሪያውኑ አባሎቻችን ሕግ ሲጥሱ መቃወም ያለብን እኛ በመሆናችን ይህንን ለማድረግ ዝግጁ ነን ብለዋል።የትግራይ ክልል ምርጫ ቋሚ የሥራ አመራሮች እስኪመደብ ድረስ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ በመድረኩ የተጠቀሰ ሲሆን፤ የአገር አቀፍ ምርጫው አጠቃላይ ውጤትም ሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም ይፋ እንደሚሆንም ታውቋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38161
[ { "passage": "ግንቦት 28/2013 ዓ.ም የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ የሚሰጥበት ቀን እንደሚሆን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አደረገ።\n", "passage_id": "67a2cc177311bed300cfe0f600622f5d" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2012 ዓ.ም. የምርጫ 2012 ጊዜያዊ የምርጫ ሰሌዳ ለውይይት አቅርቧል፡፡ ቦርዱ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ስለቀጣዩ ምርጫ ዕቅድና መርሐ ግብር ውይይት እያደረገ ሲሆን፣ ጊዜያዊ የምርጫ 2012 ዋና ዋና ቀናትና ተግባራትን ይፋ አድርጓል፡፡ በምርጫ ቦርድ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የምርጫ ክልል ቢሮዎችን ማደራጀት ከታኅሳስ 22 እስከ መጋቢት 2 ቀን 2012 ዓ.ም. የሚከናወን ሲሆን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላ ከጥር 16 እስከ የካቲት 24 ቀን 2012 ዓ.ም. ይካሄዳል፡፡ የምርጫ ክልል ካርታ ይፋ የሚደረገው የካቲት 24 ቀን 2012 ዓ.ም. ሲሆን፣ ለመራጮች ምዝገባ ትምህርትና መረጃ መስጫ ጊዜ ደግሞ ከመጋቢት 14 እስከ ሚያዝያ 28 ቀን 2012 ዓ.ም. ይሆናል፡፡ የመራጮች ምዝገባ ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዝያ 28 ቀን 2012 ዓ.ም. ሲደረግ፣ የመራጮች ምዝገባ ለሕዝብ ይፋ የሚሆንበት ጊዜ ከሚያዝያ 29 እስከ ግንቦት 8 ቀን 2012 ዓ.ም. ነው፡፡ የዕጩ ምዝገባ ሒደት መረጃ የሚሰጥበት ጊዜ ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዝያ 26 ቀን 2012 ዓ.ም. ሲሆን፣ የመወዳደሪያ ምልክት ማቅረቢያና መወሰኛ ጊዜ ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዝያ 8 ቀን 2012 ዓ.ም. ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ የዕጩ ምዝገባ ጊዜ ከሚያዝያ 13 እስከ ሚያዝያ 26 ቀን 2012 ዓ.ም. የሚደረግ ሲሆን፣ የምረጡኝ ዘመቻ ጊዜ ከሚያዝያ 27 እስከ ነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም. ይካሄዳል፡፡ የዕጩ ምዝገባ ቅሬታና የአቤቱታ ጊዜ ከሚያዝያ 13 እስከ ግንቦት 30 ቀን 2012 ዓ.ም. የሚደረግ ሲሆን፣ የድምፅ መስጫ ወረቀት ቅደም ተከተልን አስመልክቶ ፓርቲዎች ዕጣ የሚያወጡበት ቀን ሰኔ 4 ቀን 2012 ዓ.ም. ይሆናል፡፡የዕጩዎች ዝርዝር ሰኔ 7 2012 ቀን ዓ.ም. ይፋ እንደሚደረግ ቦርዱ አስታውቋል፡፡ የድምፅ መስጫ ወረቀት ኅትመት ከሰኔ 7 እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደሚካሄድ ያስታወቀው ቦርዱ፣ የድምፅ መስጫ ቀንና ውጤት ሒደትን አስመልክቶ ለመራጮች መረጃ የሚሰጥበት ጊዜ ከሰኔ 24 እስከ ነሐሴ 19 ቀን 2012 ዓ.ም. ነው፡፡ በመሆኑም ዘመቻ ዘመቻ የተከለከለበት የምርጫ  ጊዜ ከነሐሴ 6 እስከ ነሐሴ 9 ቀን 2012 ዓ.ም. ይሆናል፡፡ ምርጫ ቦርድ የድምፅ መስጫ ቀን ነሐሴ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደሚሆን ገልጾ፣ የምርጫው ውጤት በምርጫ ጣቢያዎች ይፋ የሚደረግበት ቀን ከነሐሴ 10 እና 11 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደሚሆን አስታውቋል፡፡ በዚህም መሠረት በምርጫ ክልል ደረጃ ቅድመ ውጤት ይፋ የሚሆንበት ጊዜ ከነሐሴ 11 እስከ ነሐሴ 15 2012 ዓ.ም. ሲሆን፣ የቦርዱ የተረጋገጠ ውጤት ማሳወቂያ ጊዜ ከነሐሴ 11 እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደሚሆን ታውቋል፡፡", "passage_id": "df9c328f688e7fd4f3bec5866cb46c87" }, { "passage": "አዮዋ በተባለው በመካከለኛው ምስራቅ በሚገኘው ክፍለ ግዛት ሪፖብሊካዊውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕን ሊፎካከር የሚችል ተወዳዳሪ መምረጥ ከመጀመሩ በፊት የመጨረሻ ፊት ለፊት ክርክር ይሆናል ማለት ነው። ብሄራዊ ምርጫ የሚደረገው በመጪው ህዳር ወር ላይ ነው።የቀድሞው ምክትል ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ ሴነተር በርኒ ሳንደርስ፣ ሴኔተር ኤልዝበት ዋረን፣ የኢንዲያና ከንቲባ ፒት ቡደጀጅ፣ ሴኔተር ኤሚ ክሎባሸርና ቢልዮነሩ ቶም ስተይር ናቸው ዛሬ ማታ የሚከራከሩት።", "passage_id": "8f54169197a7d6ad7383abbade734273" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዚህ ዓመት የሚካሄደውን 6ኛውን ብሄራዊ ምርጫ በተመለከተ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የውጭ አገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ገለፃ እየተደረገ ነው።የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስና የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት የውጭ ቋንቋና ዲጂታል ሚዲያ ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ማብራሪያውን በመስጠት ላይ ይገኛሉ።                                    የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ተዓማኒና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲካሄድ የተለያዩ ዝግጅቶች ተደርገዋል።በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ለተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ተደርጓልም ብለዋል።ከዚህም ባለፈ የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማሳደግ መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ስለመሆኑ ማብራራታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡ኢትዮጵያ በ2012 ዓ.ም ልታካሂደው የነበረው ብሄራዊ ምርጫ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት እንዲራዘም መደረጉ ይታወቃል።ይሁን እንጂ የጤና ሚኒስቴር የዓለም ጤና ድርጅት ያስቀመጣቸውን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት ምርጫ ማካሄድ እንደሚቻል ከተለያዩ አገራት ተመክሮ መውሰዱንም ገልጿል።የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም በጤናሚኒስቴር የቀረበለትን ምክረ ሃሳብ ተቀብሎ ምርጫው እንዲካሄድ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።", "passage_id": "f8ede25af23a14bcf9a290caa42d0976" }, { "passage": " በ1997 ዓ.ም የኢትዮጵያን 4ኛ አገራዊ ምርጫ የታዘበው የአውሮፓ ህብረት፤ መጪውን  ሀገር አቀፍ ምርጫ ለመታዘብ ማቀዱን አስታወቀ፡፡ ህብረቱ በሀገሪቱ በነሐሴ የሚካሄደውን ምርጫ እንዲታዘብ ባለፈው ታህሳስ ወር ከኢትዮጵያ መንግሥት ግብዣ እንደቀረበለት ትናንት ለጋዜጠኞች የገለፁት የአውሮፓ ህብረት የቅድመ ምርጫ ጥናት ቡድን፤ አባላት በቀጣይ 15 ቀናት ውስጥ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመዘዋወር ለምርጫው ምቹ ሁኔታ ስለመኖሩ እንደሚያጠኑ ጠቁመዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረት ምርጫውን ለመታዘብ የሚያስችለው ምቹ ሁኔታ ስለመኖሩ፣ በየትኞቹ አካባቢዎች የሚካሄድ ምርጫዎችን ቢታዘብ የተሻለ እንደሚሆን፤ ሀገሪቱ በፀጥታና ደህንነት በኩል ለምርጫው ያላትን ዝግጁነት ያጠናል ይገመግማል ተብሏል፡፡  ለዚህ ጥናትና ግምገማ ይረዳው ዘንድ ድሬደዋና ሀረርን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ምልከታ እንደሚያደርግ ቡድኑ አባላት ገልፀዋል፡፡ ከዚህም ሌላ ከጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ከመንግሥት አካላት ጋር ውይይት እንደሚያደርግ ታውቋል፡፡ አጥኚ ቡድኑ ያገኘውን ግብረ መልስ ወደ አውሮፓ ይዞ በመመለስ የመረጃ ትንተና ከሰራ በኋላ ህብረቱ ምርጫውን ይታዘብ አይታዘብ በሚለው ላይ ውሣኔ ያሳልፋል፡፡ የውሣኔው ውጤት በቀጣዩ የካቲት ወር ይታወቃል ተብሏል፡፡ ", "passage_id": "fd6eaf6b88efc9cb0a7b45cec626da60" } ]
8b2ad32a1438c10e90ffed756fb48fc3
f56301e5450eeb3bc3010d9dec47f46e
ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ለ“ትንሿ ኢትዮጵያ” ሕጋዊ እውቅና ሰጠች
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በአሜሪካዋ ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ለ“ትንሿ ኢትዮጵያ” ሕጋዊ እውቅና ማግኘቱን በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ፍፁም አረጋ በማህበራዊ ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ አስታውቁ።አምባሳደሩ እንዳስታወቁት፤ የተሰጠው እውቅና ሁለቱ አገራት ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ከማሳደግ ባሻገር በማህበራዊና በባህላዊ ዘርፉ የሚደረጉ ግንኙነቶችን ይበልጥ የሚያጠናክረው ነው።አምባሳደር ፍፁም አረጋ የዋሽንግተን ዲሲ ከተማ አስተዳደር እና የአሜሪካ የንግድ ማህበረሰብ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለ”ትንሿ ኢትዮጵያ” እውቅና እንዲያገኝ ላበረከቱት ድጋፍና አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38158
[ { "passage": "ኢትዮጵያ ውስጥ የዜጎች ሰብዓዊ መብት እንዲከበር ግፊት ለማድረግ ታልሞ ባለፈው ዓመት በየካቲት ወር መጀመሪያ ለዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት በቀረበው የሕግ ረቂቅ ቀጣይ ሂደት ዙሪያ የተካሄደ ጋዜጣዊ ጉባኤ ተንተርሶ የተጠናቀረ ዘገባ በትላንትናው ምሽት አሰምተናል።ባሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚታየው ሁኔታ ካልተለወጠ HR-128 የሚል መጠሪያ የተሰጠው ይህ ረቂቅ ሕግ ወደ ሙሉ ምክር ቤቱ ተመርቶ ሊጸድቅ የሚችል መሆኑን ነበር በምክር ቤቱ የብዙኃኑ ፓርቲ ተጠሪ በተገኙበት በተካሄደው ጋዜጣዊ ጉባኤ የተገለጸው።በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት የኮሎራዶ ክፍለ ግዛት ተወካይ ከኮንግሬስማን ማይክል ሃዋርድ ኮፍማን ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልሳቸው በእንቅስቃሴው አብረዋቸው እንደሚሰሩ ከጠቀሷቸው ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን አንዱ ናቸው።አምሳሉ ካሳው ይባላሉ። የኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን ግብረ-ኃይል ቃል አቀባይ ናቸው። ስለ ጋዜጣዊ ጉባኤው፥ ስለ ረቂቅ ሕጉ እና በኢትዮጵያ ጉዳይ ከምክር ቤት አባላቱ ጋር ስለሚሩት ሥራ ይወያያሉ።", "passage_id": "9fd3954a02983343ea6e5ac4fc855a05" }, { "passage": "ኢትዮጵያ ውስጥ በነበሯቸው እንቅስቃሴዎች፤ በዋሺንግተን ዲሲና በአካባቢዋ፣ እንዲሁም በአትላንታ-ጆርጂያ በተለያዩ የሙያ፣ የንግድ፣ የበጎ አድራጎት፣ የድጋፍና ሌሎችም ተግባሮቻቸው የሚታወቁት የአቶ ሰሎሞን በቀለ አስከሬን ዛሬ ተሸኝቷል።አቶ ሰሎሞን በቀለ ያረፉት በሰባ ስድስት ዓመት ዕድሜአቸው ሲሆን የዛሬው የሽኝትና የፍትኀት ሥርዓት የተካሄደው ሜሪላንድ በሚገኘው ደብረገነት መድኃኔዓለም ቤተክርስትያን ነው።አቶ ሰሎሞን በቀለ በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ከአዲስ አበባ የንግድ ሥራ ኮሌጅ በሂሣብ አያያዝ ተመርቀዋል። ከዚያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ በበረራ ኦፐሬሽኖች ክፍል አገልግለዋል።ወደ ዩናይትጽድ ስቴትስ በ1960 ዓ.ም. ከገቡ በኋላ በአትላንታ-ጆርጂያ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፍልሰተኛ ሆነዋል።ከክላርክ አትላንታ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ይዘዋል። በጆርጂያ ስቴት ዩኒቨርሲቲም የዶክትሬት ጥናታቸውን ለማካሄድ ገብተው ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከጆን ማርሻል ትምህርት ቤት በሕግ ዶክትሬት ዲግሪ መያዛቸውን የሕይወት ታሪካቸውን ለመዘከር የወጣ ፅሁፍ ይናገራል።አቶ ሰሎሞን በቀለ አትላንታ ላይ የመጀመሪያውንና ዛሬ እጅግ ግዙፉ የሆነውን የታክሲ አገልግሎት ኩባንያ /በአ.ዘ.አ./ በ1976 ዓ.ም. መሥርተዋል።በኢትዮጵያ ረዳት ለሌላቸው ኢትዮጵያዊያን ሲያደርጓቸው በነበሩ እንቅስቃሴዎች ሜሪ ጆይና ወገኔ ከሚባሉ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጋር ሲተባበሩ ከመቆየታቸው ሌላ በቀጥታም የረዷቸው ሰዎችና ድርጅቶች ብዙ መሆናቸው ይነገርላቸዋል።በአትላንታ ከየሳህሊተ-ምኅረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስትያን፣ በዋሺንግተን ዲሲም ከደብረገነት መድኃኔዓለም ቤተክርስትያን መሥራቾች አቶ ሰሎሞን በቀለ አንዱ ነበሩ።ስለፍትሕና እኩልነትም በነበራቸው አቋም በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ከኢዴኃቅ እስከ ቅንጅት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ የነበሩ እንቅስቃሴዎችንም በአካልም በገንዘብም ሲደግፉ መቆየታቸው ይታወሳል።ከወንድማቸው ከአቶ መርዕድ በቀለ ጋር የተደረገውን አጭር ቃለ-ምልልስ ያካተተ ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። ", "passage_id": "4a1e3bd381fc5361f8ad5f2cbc2ec0ea" }, { "passage": "ቪዲቸር ከሚባል የግል ኩባንያ ጋር ተባብሮ እየሠራ ያለው በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አዲስና ፈጣን የውክልና አሰጣጥ አገልግሎት ካለፈው ሣምንት አንስቶ ሥራ ላይ አውሏል።ይህ በኢንተርኔት ላይ የተመሠረተ የውክልና አሰጣጥ ቀድሞ ከአንድ ወር ተኩል በላይ ይፈጅ የነበረውን አገልግሎት ወደ ሁለት ቀናት ያወረደና ክፍያውንም ዝቅ ያደረገ፤ የወካይና ተወካይን በአካል መገኘትና መገናኘት የማይጠይቅ መሆኑን የቴክኖሎጂው ፈጣሪ አቶ ኬብሮን ደጀኔ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።ውክልና ሰጭዎች ወደ ኢትዮጵያ ኤምባሲ ዌብሳይት ገብተው ማመልከቻውን መሙላት እንደሚችሉ፣ የራሳቸውን የውክልና መስጫ መልዕክት በተቀመጠው መሠረት ከእጅ ስልካቸው በቪድዮና በድምፅ መቅረፅ፣ የሚጠየቁ ሠነዶችንም ፎቶ አንስተው ማስገባት እንደሚኖርባቸው አቶ ኬብሮን አብራርተዋል።ለሙሉው ዝርዝር የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። ", "passage_id": "c83bcccd1b21abaf4679575d8f89d689" }, { "passage": "በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የምትመራው ኢትዮጵያ ወደ ፍትህና ትክክለኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እያመራች ነው፣ “ልንደግፈው ይገባል” የሚሉ ድምፆች ከየአቅጣጫው፣ ከኢትዮጵያም ከኢትዮጵያ ውጪም እየተሰሙ ናቸው። የሰሞኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩን የዩናይትድ ስቴትስ ጉብኝት በተመለከተ፣ የኢትዮጵያው ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “ዲፕሎማሲያዊ ስኬት” ብሎታል። ይህን የተሳካ አመራር ነው ኢትዮጵያውያን በእያሉበት እየደገፉና እያበረታቱ ያሉት። በአሁኑ ሰዓት፣ ካናዳ ኦታዋ የሚገኘው የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላትም ይህንኑ ነው እያደረጉ ያሉት።። ", "passage_id": "5380b4eb52645d4ad3e327b747d63d52" }, { "passage": "ከአርቲስት ሃጫሉ ግድያ በኋላ ሥልሳ ሰባት ምዕመናኗ ሆን ተብሎ በተቀነባበረና በተደራጀ አሠራር ተገደሉብኝ ስትል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አቤቱታ አሰምታለች።የኦሮምያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥትና ፌዴራሉ መንግሥት የኦርቶዶክስ ኢትዮጵያውያንን ሰብዓዊና የዜግነት መብቶች እንዲያስከብሩ አሳሰበች።\n", "passage_id": "d9841614faba7ce40cad639027f528b2" } ]
3617ec1fb8484e313a3e070ca558d84d
849ea38013e759d393125c8ca749680c
መረጃ ፈላጊዎች ባሉበት ሆነው መረጃ ማግኘት የሚችሉበት የተቀናጀ የመረጃ ሥርዓት ይፋተደረገ
መላኩ ኤሮሴቢሾፍቱ፡- የመረጃ ፈላጊዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በይነ መረብን በመጠቀም የተለያዩ መረጃዎችን ማግኘት የሚችሉበት የተቀናጀ የመረጃ ሥርዓት ይፋ ተደረገ፡፡አዲሱን የተቀናጀ የመረጃ ሥርጭት ሥርዓቱን የፌዴራል፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ሴክተር መሥሪያ ቤቶች እንዲጠቀሙበት ለማድረግና ሥርዓቱን የማስተዋወቅ ሥልጠና መርሃ ግብር በማዕከላዊ ስታትስቲክ ኤጀንሲ እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፖፑሌሽን ፈንድ (UNF­PA) ትብብር በቢሾፍቱ ተካሂዷል፡፡በስልጠና መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አሳልፈው አበረ እንደተናገሩት፤ ከዚህ በፊት በነበረው የመረጃ ሥርጭት ሥርዓት የመረጃ ተጠቃሚዎች በአካል በማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ በመገኘት በወረቀት፣ በሲዲ እና በፍላሽ መረጃዎችን ሲቀበሉ ነበር፡፡ ይህ ሥርዓት ዘመኑ ከደረሰበት ቴክኖሎጂ አንፃር አዋጭ ባለመሆኑ አዲስ የተቀናጀ የመረጃ ሥርጭት ሥርዓት ተዘጋጅቷል፡፡አዲስ ይፋ የተደረገው ሥርዓት ውስጥ ማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ የሚያሰባስባቸው ሳይንሳዊ እና ደረጃቸውን የጠበቁ መረጃዎች እንዲሁም ክልሎች የሚያጠናቅሯቸው የአስተዳደር መረጃዎች ተዓማኒነታቸው እና ጥራታቸው ተረጋግጦ የሚቀመጥ ይሆናል፡፡ በዚህም የቴሌኮም መሠረተ ልማት ባለበት በየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢ የሚገኝ ዜጋ አዲስ ወደ ተዘጋጀው ድረ ገፅ በመግባት የሚፈልገውን መረጃ መጠቀም ይችላል፡፡እንደ አቶ አሳልፈው ማብራሪያ፤ የመረጃ ተጠቃሚዎች በአዲሱ ሥርዓት ውስጥ በመግባት የናሙና ጥናት፣ የቆጠራ፣ የአስተዳደር መዛግብት እና ከሌሎች ምንጮች የተሰበሰቡ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ እና ለሚፈልጉት ዓላማ እንዲጠቀሙ ያስችላቸዋል፡፡ሥርዓቱም በሥራ፣ በትምህርት ቤት እንዲሁም በሌሎች ቦታዎች ሆነው የሚፈልጉትን መረጃ ከተቀናጀ የመረጃ ሥርዓት አውጥተው እንዲጠቀሙ የሚያስችል በመሆኑ፤ ከዚህ ቀደም የመረጃ ተጠቃሚዎች መረጃ ከኤጀንሲው በአካል መጥተው ለመውሰድ በሚያደርጉት ጥረት ያጋጥማቸው የነበረ እንግልት እና ጉዞ የሚያስቀር መሆኑን ነው አቶ አሳልፈው ያብራሩት፡፡ከዚህም ባሻገር መረጃ ለመውሰድ በሚደረገው እንቅስቃሴ ይጠፋ የነበረው ጊዜ፣ ጉልበት እና ገንዘብ ለመቆጠብ የሚያስችል ሲሆን፤ ሥርዓቱ የመረጃ ተጠቃሚዎችን እርካታ ከማሳደግ ባሻገር፤ መሥሪያ ቤቱ የተጣለበትን ተልዕኮ ለመወጣት እንደሚያስችለውም አስረድተዋል፡፡እንደ አቶ አሳልፈው ማብራሪያ፤ ሥርዓቱ በርካታ መረጃዎችን የመያዝ አቅም ያለው ነው፡፡ ከዚህ በፊት የነበሩ መረጃዎችንም ወደዚህ ሥርዓት ውስጥ የማስገባት ሥራ እየተሠራ ነው፡፡ እስካሁን ድረስ የ1987 እና የ1999 የሕዝብና ቤት ቆጠራ መረጃዎች ገብተዋል፡፡ እነዚህ መረጃዎች በዚህ ሥርዓት ውስጥ መግባታቸው ትልቅ ፋይዳ አላቸው፡፡ለተለያዩ ዓላማዎች የተለያዩ መረጃዎችን የሚፈልጉ ግለሰቦች እና ተቋማት ከአሁን ጀምሮ ከአዲሱ ሥርዓት መረጃ በመውሰድ መጠቀም እንደሚችሉም አቶ አሳልፈው ጠቁመዋል፡፡የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፖፑሌሽን ፈንድ ተወካይ አቶ አለማየሁ ገብረጻድቅ በበኩላቸው፤ ሥርዓቱን የመዘርጋት ሥራ ዓመታትን እንደወሰደ ገልፀው፤ አማራ እና ደቡብ ክልል ሥርዓት በመዘርጋት ጥሩ ጅምር ማሳየታቸውን አብራርተዋል፡፡ አንዳንድ የውጭ ተቋማት ጭምር መረጃዎችን ከአዲሱ ሥርዓት ወስደው እየተጠቀሙ መሆኑን በመጠቆምም፤ ሌሎች ክልሎችም በአጭር ጊዜ ውስጥ አሠራሩን ወደ መተግበር እንዲገቡ ይሠራል ብለዋል፡፡አዲሱ የመረጃ ማሰራጫ ሥርዓት ከዚህ ቀደም ከነበረው ጋር ሰፊ ልዩነት እንዳለው የጠቆሙት አቶ አለማየሁ፤ በአዲሱ ሥርዓት አንዴ መረጃው ወደ ሥርዓቱ ውስጥ ከገባ መቀየር የማይቻል መሆኑ ለየት እንደሚያደርገው አብራርተዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38159
[ { "passage": "የሕግ ጽሑፎችን ወይም የሕግን መረጃን ማግኘት አዳጋች መሆኑን የፍትህና የሕግ ምርምር ስልጠና ኢንስቲትዩት ያካሄደው ጥናት አመለከተ፡፡\nኢንስቲትዩቱ በ2011 በጀት ዓመት የሕግ ጽሑፎችን ወይም የሕግን መረጃ ማግኘት በተመለከተ ባደረገው ጥናት ችግሩን መሻገር እንዳልተቻለ ዛሬ ከባለድርሻ አካላት ጋር እያከናወነው ባለው የምክክር መድረክ ላይ ተገልጿል፡፡\nየኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ የህግ ተመራማሪ ወ/ሮ የትናየት ደሳለኝ ጥናቱን ሲያቀርቡ እንደገለፁት ጥናቱ በፌዴራል ደረጃ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች፣ የፖሊስ ኮሚሽን ፍርድ ቤቶችና ጠቅላይ አቃቤ ሕግ እንደተከናወነና በቀጣይም ችግሮቹን ለመቅረፍና የመንግስት ፖሊሲን ለመደገፍ ያስችላል፡፡\nሕግና ሕግ ነክ መረጃዎች ያላቸውን ልዩ ባሕሪይ ታሳቢ ያደረገ የህግ ማዕቀፍ አለመኖር፣ አማራጭ የመረጃ መስጫ መንገዶች በተገቢው ሁኔታ ተደራሽ አለመሆን፣ መረጃ ማግኘት በግለሰቦች መልካም ፈቃድኝነት ላይ የተመሰረተ መሆኑ፣ ብቁ የሆኑ ባለሙያዎች አለመኖራቸው እና የግንዛቤ እጥረት ለችግሩ መባባስ ጥናቱ የለያቸው ምክንያቶች ናቸው፡፡\nበፍትህ ተቋማት የሚገኙ ቤተመጽሐፍት ከሌሎች የሕዝብ ቤተመጽሐፍት ጋር በመስራት ሕግና የሕግ መጽሐፍተን ተደራሽ ማድረግ፣ መረጃ መስጫ ሱቆችን መክፈት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ሕብረተሰቡ በስፋት እንዲሳተፉ ማድረግ የሚሉት ደግሞ ጥናቱ በመፍትሔነት ያስቀመጣቸው ሐሳቦች እንደሆኑ ወ/ሮ የትናየት አመልክተዋል፡፡\nበምክክር መድረኩ “የእርሻ መሬት ይዞታና የማስተላለፍ መብት” በሚለው የመወያያ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ዜጎች ባላቸው የመሬት ይዞታ ዋስትና ተገቢውን የሕግ ከለላ አለማግኘታቸው ተገልጿል፡፡\nበአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ትግራይ እና ደቡብ ሕዝቦች፣ ብሄሮችና ብሄረሰቦች ክልሎች በተደረገው ጥናት ወደ ፍርድ ቤት ከሚመጡ የፍትሃብሄር ጉዳች ውስጥ 70 በመቶ የሚሆኑት የእርሻ መሬት ይዞታን የሚመለከቱ ስመሆኑ በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡\nበሕገመንስግሰቱ አንቀፅ 40 ንዑስ ቁጥር 4 ላይ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬት በነፃ የማግኘት መብት ብቻ ሳይሆን ከመሬታቸው ያለመፈናቀል መብት አላቸው ሲል ቢደነገግም ይህ መብታቸው ግን እምብዛም ሲከበር አይታይም ተብሏል፡፡\nየአርሶ አደሩ የእርሻ መሬት በህግ ከተቀመጠው ውጪ በባህልና በተለምዶ ማስተላለፍ፣ ከህግ ውጪ ያሉ አሰራሮችና ክፍተቶች መበራከት፣ የተደራጀ የእርሻ መሬት አያያዝ ሥርዓት አለመዘርጋት፣ ህጎች መብትን የሚሰጡት ለክልሎች ነዋሪዎች በመሆኑ የዜጎችን ተዘዋውሮ የመስራት መብት የገደቡ መሆናቸው በጥናቱ የተመለከቱ ችግሮች ናቸው፡፡\nከመሬት ጋር በተያያዘ የሚሰሩ ባለሙያዎችን በቂ ዕውቀት እንዲኖራቸው ማድረግ፣ የገጠር መሬት ጉዳይን ሊዳኝ የሚችል ራሱን የቻለ ተቋም መፍጠር፣ ለልማት ለሚነሱ አርሶአደሮችን የሚሰጣቸውን የገንዘብ ካሳ ተለዋጭ ቦታ በመስጠት ቢሆን እና ከገጠር መሬት ጋር ያለ መረጃ የተደራጀና በቴክኖሎጂ የታገዘ ቢሆን የሚሉት ደግሞ ጥናቱ በመፍትሄ ሐሳብነት ያመላከታቸው መሆኑን በምክከር መድረኩ ላይ ተነስቷል፡፡", "passage_id": "5cd628744fedba1319260c458201a5e6" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- የኢንተርኔት ማቆም፣ መረጃን አጣርቶ ማውጣትና መዝጋት በተመለከተ በአገር ደረጃ የወጣ ህግ ባለመኖሩ ተገቢው መረጃ ለተገቢው አካል እንዳይደርስ ሆኗል። በዚህም ይህንን ለማረም በኮምፒውተር ወንጀሎች አዋጅ ለማካተት ረቂቅ እየተዘጋጀ መሆኑን የብሔራዊ ህግና ፍትህ አማካሪ ምክርቤት አስታወቀ።በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት መምህርና በጠቅላይ አቃቤ ህግ የተቋቋመው የህግና ፍትህ አማካሪ ምክርቤት አባል ረዳት ፕሮፌሰር መሰንበት አሰፋ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ መንግስት ኢንተርኔትን በማቆም፣ በመዝጋትና መረጃ አጣርቶ በማውጣቱ ዙሪያ ሊከተላቸው የሚገቡ ህጎች በአገር ደረጃ አልተቀመጡም። በዚህም በተለያየ መንገድ እነዚህ ክዋኔዎች ተግባራዊ እየሆኑ መጥተዋል። ይህ ደግሞ ተጠቃሚዎችንም ሆነ ህዝቡን መረጃ በትክክል እንዳያገኝ አድርጎታል። በሚዲያ የመረጃ ነጻነትና\nበኮምፒውተር ወንጀሎች ረቂቅ\nአዋጅ ዙሪያ አሁን\nባለው ደረጃ ምክር\nቤቱ ከባለድርሻ አካላት\nጋር በመወያየት ህግ\nለማውጣት እየሰራ እንደሆነ\nየሚገልጹት ረዳት ፕሮፌሰሩ፤\nየህጉ መውጣት በህግ\nአግባብ የተቃኘ መረጃ\nለህዝብ እንዲደርስ እድል\nይሰጣል ብለዋል። የኢንተርኔት\nአጠቃቀም ሁኔታውም ሥርዓት\nእንዲኖረው ያደርጋል። ከዚያ\nባሻገር መንግስት ምን\nምን አስገዳጅ ሁኔታ\nሲገጥመው ኢንተርኔትን ማቆም፣\nመዝጋትና ትክክለኛ መረጃ\nአውጥቶ  ማሰራጨት እንዳለበትም ያመላክታል። ከዚያ ውጪ ከተሰራ ደግሞ ተጠያቂነት እንዲኖርበት ያደርጋል። በተመሳሳይ ተጠቃሚ አካላትም የህግ አግባብን ተከትለው አቤቱታቸውን እንዲያቀርቡ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል። በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት የመገናኛ ብዙሃን ህግ መምህርና በኔቶርክ ፎር ዲጅታል ራይት አባል ዮሐንስ እንየው በበኩላቸው፤ አገሪቱ በተለያየ መልኩ በቴክኖሎጂ እያደገች ከመምጣቷ ጋር ተያይዞ ብዙ ወንጀሎች ይፈጸማሉ። በዚህም ይህ ህግ አለመኖሩ ወንጀሉ እንዲበራከት ያደርጋልና ህጉ እንዲወጣ መታሰቡ የመረጃ ትክክለኛነትን ከማረጋገጥ አኳያ የማይተካ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። በኮምፒውተር ወንጀሎች አዋጅ ውስጥ ተካቶ ተጠያቂነት እንዲኖር መደረጉ ግን አጠያያቂ እንደሆነ የሚጠቅሱት መምህር ዮሐንስ፤ ኢንተርኔት ከለውጥ በፊትም ሆነ በኋላ እየተዘጋ ነው። አሁንም ዝግ የሆነባቸው ቦታዎች አሉ። ስለሆነም ለምን ተዘጋ የሚለውን በደንብ ግልጽ ማድረግና ከኮምፒውተር ወንጀል አዋጁ ጋር ማገናኘት ያስፈልጋል ብለዋል። ተፈጻሚነቱንም ማፋጠን እንደሚገባ አሳስበዋል። ምክንያታቸውም በቅርብ በወጣው የኢትዮ ቴሌኮም መረጃ 22 ነጥብ 74 ሚሊዮን ህዝብ ኢንተርኔት ይጠቀማል። በዚህ አዋጅ ውስጥ የሚካተቱ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ጥርት ባለ መልኩ መጻፍና መተግበር እንዳለባቸው የሚናገሩት መምህር ዮሐንስ፤ ሁኔታው በፍጥነት ተጠናቆ በህግና መመሪያ ታስሮ ወደ ትግበራ መግባት እንዳለበት አስረድተዋል።አዲስ ዘመን ጥር 24/2012ጽጌረዳ ጫንያለው", "passage_id": "6479c0a2308ac7189b5975118b44a447" }, { "passage": "– በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የጋራ መኖሪያ፣ የንግድ እና የቀበሌ ቤቶች ቆጠራና አጠቃላይ መረጃ የማሰባሰብ ስራ ሊካሄድ ነው።የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን መንግስቱ ፤ መረጃ የመሰብሰቡ ስራ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ  የሚጀመር ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ሲካሄድ ከነበረው በተለየ መልኩ የሚፈጸም ይሆናል ብለዋል። ኤጀንሲው ቤቶችን የመቁጠር እና መረጃ የማጠናከር ስራ በየአመቱ እያካሄደ ቢገኝም ከሚያስተዳድራቸው 146 ሺህ የቀበሌ እና 28 ሺህ የንግድ ቤቶች ለተጠቃሚዎች የተላለፉት 110 ሺህ ብቻ መሆናቸውን ገልፀዋል። ቀሪዎቹ አለአግባብ የተያዙ ፣ የተለያዩ ህገ ወጥ ተግባራት የሚፈጸምባቸው እና ያለጥቅም የተቀመጡ ቤቶች በመሆናቸው መንግስት ክትትሉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ለዚህም በዚህ አመት የሚተላለፉ 50 ሺህ ቤቶችና  እየሰፋ የሚሄደውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፕሮግራምን ጨምሮ ፥ የቀበሌ መኖሪያ ቤቶች እንዲሁም የንግድ ቤቶችን መረጃ አያያዝ ጋር ተያይዞ የሚፈጠረውን ችግር ለማስቀረት ኤጀንሲው የመረጃ አያያዝ ስርአቱን ዘመናዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኤጀንሲው ይህንን የቀበሌ ፣ መኖሪያ ፣ የንግድና የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ቆጠራና መረጃ የመሰብሰብ ስራ ለመጀመር በአሁን ጊዜ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያካሄደ ሲሆን፥  መረጃው በአዲስ መልክ መሰብሰቡም ለፖሊሲ አውጪዎች ግብአት ከመሆኑ ባለፈ በህገወጥ መንገድ የተያዙ ቤቶች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ያስችላል ነው ያሉት።", "passage_id": "5c971e534f0842a333a9cb679476f2f0" }, { "passage": "የግብርናና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ በሀገሪቱ ያለውን የአፈር ሁኔታን የሚያሳዩ መረጃዎችን  በማእከላዊ የመረጃ ቋት ማሰባሰቡን የኤጀንሲው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ካሊድ ቦምባ ተናግረዋል።በዚህ የመረጃ ማሰባሰብና የጥናት ሂደትም በወረዳና በቀበሌ ደረጃ የአፈር ለምነትና ለአፈሩ የሚያስፈልገው የማዳበሪያ አይነት በካርታ በተደገፈ መልኩ ለአብዛኛው ክልሎች መድረሱን የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው።የዚህ የመረጃ ማሰባሰብና የጥናት ሂደትም 95 በመቶ መጠናቀቁንና ቀሪዎቹ እስከ መስከረም እንደሚጠናቀቁ ተናግረዋል።የዚህ ጥናት ዋና አላማው በሀገሪቱ ዘላቂነት ያለው ምርታማነትን ማምጣት እንደመሆኑ መጠን ከተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመሆን መስራት እንደሚያስፈልግና ፡አርሶ አደሩን ተጠቃሚ እንዲሆን በማድረግ አፈርን መጠበቅ እንደሚያስፈልግም ተነግሯል።ያነጋገርናቸው የውይይቱ ተሳታፊዎች ጥናቱ አበረታችና የኢትዮጵያን የአፈር መረጃ ቋት እንዲኖራት የሚያስችል መሆኑን ገልፀው በሀገሪቱ ዘላቂነት ያለው ምርታማነትን ለማምጣት ባለድርሻ አካላት በጋራ መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል", "passage_id": "b26f0a7e312fa47673bd704813e4b8a0" }, { "passage": "የመንግሥት አካላት በአምስት ቀናት ለሚዲያዎች ምላሽ እንዲሰጡ የሚል ድንጋጌ ይዟልየመንግሥት አካላትን የሐሳብ ልውውጥ ሊያሰናክል የሚችል መረጃ ክልከላ ይጣልበታልየመረጃ ነፃነት ኮሚሽን እንደሚቋቋም ይገልጻልየመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ የሕግ ማሻሻያ ሪፎርሞች አካል የሆነው ረቂቅ የመረጃ ነፃነት አዋጅ ለባለድርሻ አካላት ውይይት ቀረበ።በዓቃቤ ሕግ ሥር የተቋቋመው የሕግ ማሻሻያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት አማካይነት ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት፣ በምክር ቤቱ ሥር ተደራጅቶ አዋጁን ካረቀቀው የባለሙያዎች ቡድን ጋር ማክሰኞ መስከረም 12 ቀን 2013 ዓ.ም. በረቂቅ ሰነዱ ላይ ውይይት አድርገዋል።ለውይይት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ስለመረጃ ነፃነት አስፈላጊነት የሚገልጹ ማብራሪያዎችን በመግቢያ ሀተታው ላይ ያስቀመጠ ሲሆን፣ የመረጃ ነፃነትን በማረጋገጥ ሰብዓዊ መብቶችን ማረጋገጥ፣ በሕዝብና በመንግሥት መካከል መልካም ግንኙነትን መገንባትና ሙስናን መዋጋት አስፈላጊ እንደሆነ ያስረዳል።የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 29(3)(ለ) መረጃ የማግኘት መብትን በግልጽ ያረጋገጠ በመሆኑና የኢትዮጵያ መንግሥት የአስተዳደር ባህል በአብዛኛው ሚስጥራዊ በመሆኑ ሥልጣንን ያላግባብ መጠቀምንና የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ማስከተሉን በመረዳት፣ እንዲሁም የሕዝብ ጥቅምን የሚመለከቱ ጉዳዮች ግልጽ እንዲደረጉና ውይይት እንዲደረግባቸው ግልጽ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ ማበጀት አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት ረቂቁ መሰናዳቱን የረቂቁ መግቢያ ይገልጻል።የመንግሥትና የግል አካላት ለግለሰቦችና ለመገናኛ ብዙኃን መረጃን ተደራሽ እንዲያደርጉ የሕግ ግዴታ ለመጣል፣ የሕዝብ ተሳትፎንና የሥልጣን ባለቤትነትን የማረጋገጥ፣ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ውጤታማነት የሰፈነበት የመንግሥት አሠራርንና መልካም አስተዳደርን ለማጠናከር በመወሰንና የመረጃ ነፃነትን ማረጋገጥ ያለውን ከፍተኛ ሚና በመገንዘብ ረቂቁ መሰናዳቱንም ያስረዳል።በዚህም ምክንያት በሥራ ላይ ያለውን የመረጃ ነፃነት ሕግ በማሻሻል የሕዝቡን መረጃ የማግኘት ፍላጎት በሚያንፀባርቅና መብቱን ይበልጥ መጠበቅና ማራመድ በሚያስችል አዲስ ሕግ መተካቱ አስፈላጊ መሆኑ በረቂቁ መግቢያ ተመልክቷል።በረቂቁ ከተካተቱ ድንጋጌዎች መካከል በመገናኛ ብዙኃን ለሚቀርብ መረጃ የማግኘት ጥያቄ የመንግሥት አካላት ግዴታና ኃላፊነቶችን ያስቀመጠ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ለመገናኛ ብዙኃን የመረጃ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡበትን የጊዜ ገደብ ይወስናል።የመገናኛ ብዙኃን ወይም መረጃን ለሕዝብ ማሠራጨት ዋነኛ ተግባሩ የሆነ አመልካች፣ በመንግሥት አካል ተከናውኗል ወይም በቅርቡ ሊከናወን ነው የሚባልና ሕዝብ በአስቸኳይ ሊያውቀው የሚገባ መረጃ ስለመሆኑ ተጨባጭ ምክንያታዊ መነሻ ያለው ጥያቄ ካቀረበ፣ የመንግሥት አካሉ እጅግ ቢዘገይ ከአምስት የሥራ ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ምላሽ መስጠት እንዳለበት በረቂቅ አዋጁ ተደንግጓል።ይሁን እንጂ ይህ የመረጃ ጥያቄ የቀረበለት የመንግሥት አካል የመረጃ ኃላፊ የቀረበው የመረጃ ጥያቄ አጣዳፊ አይደለም ብሎ ካመነ፣ አመልካቹ አስተዳደራዊ ይግባኝ ማቅረብ እንደሚችል ምላሽ በመስጠት የመረጃ ጥያቄውን በ20 የሥራ ቀናት እንዲያስተናግድ ይደነግጋል።መረጃ ጠያቂው በውሳኔው ካልተስማማ ለተቋሙ የበላይ አመራር አቤቱታ ማቅረብ እንደሚችል፣ በበላይ አመራሩ ውሳኔ ቅር ከተሰኘም ለመረጃ ነፃነት ኮሚሽኑ ቅሬታ ሰሚ አቤቱታውን ማቅረብ እንደሚችል፣ በዚህም መረጃ የማግኘት መብቱ እንደተነፈገ ካመነ ለፍርድ ቤት ይግባኝ ማቅረብ እንደሚችል የሚገልጹ ድንጋጌዎችን ረቂቁ አካቷል።አቤቱታ የቀረበለት የበላይ አመራር ለአስቸኳይ የመረጃ ጥያቄ በአምስት የሥራ ቀናት ውሳኔ መስጠት እንዳለበት፣ በተመሳሳይ ለኮሚሽኑ በቀረበ የአስቸኳይ መረጃ ጥያቄ አቤቱታ ላይ ኮሚሽኑ በአምስት የሥራ ቀናት ምላሽ መስጠት እንዳለበት፣ የተገለጹትን ሒደቶች አልፎ ለፍርድ ቤት በሚቀርብ ይግባኝ ላይ ደግሞ፣ ፍርድ ቤቱ በ30 ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት እንደሚኖርበት ረቂቅ ድንጋጌዎቹ ያመለክታሉ።የአዋጁን ዓላማዎች ለማስፈጸም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የሚሆን የመረጃ ነፃነት ኮሚሽን እንደሚቋቋምም የረቂቁ ድንጋጌ ያመለክታል።\n\nየኮሚሽኑ አባላት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚያቋቋመው ገለልተኛ ኮሚቴ አማካይነት በረቂቁ የተገለጹ መሥፈርቶች ተመዝነው ብቁ የሆኑት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚቀርቡ ተመልክቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ መሠረት ከሚቀርቡለት የኮሚሽኑ አባላት መካከል ዋናና ምክትል ኮሚሽነሮችን በመምረጥ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሾሙ የሚያቀርብ መሆኑን የረቂቁ ድንጋጌዎች ያመለክታሉ።ለመረጃ ጠያቂዎች የማይሰጡ ወይም ጥበቃ የሚደረግላቸው መረጃዎችና ሰነዶችንም ሪቂቅ አዋጁ ይዘረዝራል። ከእነዚህም መካከል ጥበቃ የሚደረግላቸው የመንግሥት የሥራ ሰነዶችና መረጃዎች ምንነትና ክልከላ የሚጣልበትን አመክንዮ የሚዘረዝሩ ይገኙበታል።በዚህም መሠረት የመረጃው መገለጽ ግልጽ የሆነ የሐሳብ ልውውጥን፣ ምክክርን፣ ሪፖርትን፣ የውሳኔ ሐሳብን ወይም ውይይትን በመገደብ በማንኛውም የመንግሥት አካል ውስጥ ወይም በተለያዩ የመንግሥት አካላት መካከል የሚደረገውን የውይይት፣ ወይም የምክክር ሒደት ሊያስተጓጉል እንደሚችል የመረጃ ኃላፊው ያመነበትን የመንግሥት ሰነድ መከልከል እንደሚችል ይደነግጋል።መንግሥት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ለማስተዳደር ያለውን አቅም ሊያዳክሙ የሚችሉ፣ የመንግሥት ድርጅቶችን የንግድ እንቅስቃሴዎች የሚመለከቱ መረጃዎች እንዳይገለጹም የመረጃ ኃላፊው ጥበቃ ማድረግ ይችላል።በሥራ ላይ ያለው የብድር ወይም የወለድ ተመንን፣ የጉምሩክ ወይም የኤክሳይስ ቀረጥን፣ የግብር ወይም ማናቸውም ሌላ የመንግሥት የገቢ ምንጮችን፣ የመንግሥት የፋይናንስ ተቋማት ቁጥጥርን ወይም ክትትልን፣ የመንግሥት ብድርን፣ የሸቀጦች ወይም የአገልግሎቶች ዋጋን፣ የኪራዮችን፣ የደመወዝ ወይም የቀን ክፍያዎችን ወይም ሌሎች ገቢዎችን የሚመለከቱ ቁጥሮችን የመለወጥ ወይም እንዳለ የመቆየት ውሳኔ ውጥኖችን እንዳይገለጹ ጥበቃ ከሚደረግላቸው መረጃዎች መካከል ናቸው።በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት ክልከላ የሚጣልባቸው ወይም ጥበቃ የሚደረግላቸው መረጃዎች በተመለከተ የተቀመጠው የረቂቁ ድንጋጌ ለትርጉም የተጋለጠ በመሆኑ፣ ተፈጻሚነቱን አስቸጋሪ ያደርገዋል የሚል ሥጋታቸውን ገልጸዋል።ለመረጃዎች ጥበቃ እንዲደረጉ ተብለው የተገለጹት ምክንያቶች፣ ‹‹ማስተጓጎል ወይም ማሰናከል›› የሚሉ መሆናቸው ለትርጉም ክፍት እንደሆነ ገልጸዋል።ገለልተኛ የመረጃ ነፃነት ኮሚሽን እንዲቋቋም በረቂቁ መቀመጡ ከቀደመው አዋጅ ትልቅ መሻሻል የታየበት እንደሆነ የጠቀሱት ተወያዮች፣ ይህ ድንጋጌ የመፅደቅ ዕድሉ ላይ ግን ሥጋት እንዳላቸው ገልጸዋል።በረቂቅ አዋጁ ላይ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በተደጋጋሚ ጊዜ ቢዘጋጅም የባለድርሻ አካላት በተለይም የሚዲያ ባለሙያዎች ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆኑን፣ በሕግ ማሻሻል ብሔራዊ ምክር ቤቱ ሥር የተዋቀረው የሚዲያ ሕግ ሪፎርም ቡድን አስተባባሪ አቶ ሰለሞን ጎሹ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በተሳታፊዎች የቀረቡት ጠቃሚ አስተያየቶች እንደሚካተቱና በረቂቅ አዋጁ ላይ ተጨማሪ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር ወደፊት እንደሚካሄድ አቶ ሰለሞን ገልጸዋል።", "passage_id": "4b368645f08585b901639b502a8af2f5" } ]
9d4dceaf4e1fe83473f1ddca19a96ce0
fa97e08d8bbff111a391166eb02bb2c3
መቀሌ ያሉ የመንግሥት መሥርያ ቤቶች ህዝብ እንዳያገለግሉ በህወሓት ጁንታ ሆን ተብለው እንዲዘረፉና እንዲወድሙ ተደርጓል ሲሉ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
 አማን ሚካኤል መስፍንመቀሌ፡- መቀሌ ያሉ የመንግሥት መሥርያ ቤቶች ህዝብ እንዳያገለግሉ በህወሓት ጁንታ ሆን ተብለው እንዲዘረፉና እንዲወድሙ ተደርጓል ሲሉ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ዛሬ በሰማዕታት አደራሽ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት፤ በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የደረሰው ክህደትና ጥቃት ያወገዙት የከተማዋ ነዋሪዎች፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በአጭር ጊዜ ሕግ የማስከበሩን ሥራ በማጠናቀቁ አመስግነዋል። በአንፃሩ መቀሌ ያሉ የመንግሥት መሥርያ ቤቶች ህዝብ እንዳያገለግሉ በህወሓት ጁንታ ሆን ተብለው እንዲዘረፉና እንዲወድሙ ተደርጓል፤ በዚህም ህብረተሰቡ እየተጉላላ ይገኛል። የህወሓት ጁንታ በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ የነበሩ የሕግ ታራሚዎችን ሆን ብሎ በመቀሌ በትኖ ሄዷል ያሉት ተወያዮቹ፤ በእነዚህ ከማረሚያ ቤት ሆን ተብለው በተለቀቁ የሕግ ታራሚዎች ምክንያት በከተማው የፀጥታ ችግር እንዲፈጠር ተደርጓል ሲሉም ነው ያስታወቁት። የሀሰት ወሬ በመቀሌ ከተማ እየተነዛ ህዝቡ እየተሸበረ ስለሆነ አስተዳደሩ ይሄን ያጥራልን ያሉት የከተማዋ ነዋሪዎች፤ ነጋዴው ከመሃል አገር ሸቀጥ እንዳያመጣ “ጦርነት አላለቀም” በሚል ወሬ እየተነዛ ወደ ሥራ እንዳይገባም አድርገውታል ነው ያሉት።በአገር ውስጥም ይሁን በውጭ ያሉ የትግራይ ተወላጆች ጊዚያዊ አስተዳደሩንም ሆነ ህዝቡን ማገዝ አለበት ያሉት ተወያዮቹ፤ በደቡብ ትግራይ እና ምዕራብ ትግራይ አካባቢ ያሉ ጉዳዮች በሰላማዊ መንገድ መፈታት አለበት ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል። የሰሜን ዕዝ አዛዡ ጄነራል በላይ ስዩም በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መከላከያ የአገር ዳር ድንበርን የሚያስከብር ሃይል ነው። ነገር ግን ጁንታው የገደለው ይሄንን ሃይል ነው በማለት የተፈፀመውን ክህደትና ግፍ ለተወያዮቹ አብራርተዋል። “እንደመከላከያ ጓዶቻችን በጁንታው ተገድለዋል፣ የሠራዊቱ ንብረት ተዘርፏል፤ እንደ አገርም በኢኮኖሚው ላይ አሉታዊ የሆነ ተፅዕኖ ተፈጥሯል” ያሉት ጄነራሉ፤ የዘጠና ዓመት አዛውንቶች መጥተው ይመሩናል ብላችሁ ተስፋ እንዳታደርጉ፤ በእርግጠኝነት የምነግራችሁ ጁንታው ከዚህ በኋላ አይመለስም፤ ስለዚህ ተረጋግታችሁ ጊዚያዊ አስተዳደሩን ማገዝ አለባችሁ” ሲሉም ለመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።በውይይት መድረኩ ላይ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ፣ የመቀሌ ከንቲባ አቶ ኣታኽልቲ ሃይለሥላሴ እና የሰሜን ዕዝ አዛዥ ጀነራል በላይ ስዩም የተገኙ ሲሆን፤ በወቅቱም የትግራይ ህዝብ የህወሓት ጁንታ ተመልሶ ይመጣል ከሚል ሃሳብ መውጣት እንዳለበት የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶክተር አብረሃም በላይ ተናግረዋል፡፡በዚሁ መድረክ ላይ ለተነሱ የከተማዋ ነዋሪዎች ምላሽ እየሰጡ ካሉት አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራሩ ዶክተር አብረሃም በላይ እንዳሉት፤ በከተማዋም ሆነ በሌሎች ቦታዎች ላይ የህወሓት ጁንታን በተመለከተ “ተመልሰው ይመጣሉ” የሚል የሀሰት ወሬ እየተሰራጨ ይገኛል። ይህ የተሳሳተ መሆኑን ህዝቡ ማወቅ አለበት።ህዝባችን በውሸት ሊደናገር አይገባም ያሉት ዶክተር አብረሃም፤ ድሮ ጃንሆይ ከወረዱ በኋላ ህዝቡ ይመለሳሉ ብሎ ሲጠብቅ ነበር፤ ደርግም ከወደቀ በኋላ ይመለሳል ብሎ የሚጠብቅ ሰው ነበር። አሁንም እንደዛ እየጠበቀ ያለ ሰው አለ። ይህ መሆን የለበትም” ሲሉ ተወያዮቹ ላቀረቡት ጥያቄ መልስ ሰጥተዋል። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ የመንግሥት ሠራተኛ ማለት የህዝብ አገልጋይ ነው፤ ሁሉም ወደ ሥራው ገብቶ ከልብ ማገልገል አለበት። በፊት ህዝብ ያሰቃዩ፣ ጥሩ ሥነ ምግባር የሌላቸው ማልያ ቀይረው ወደ አመራር እንዳይመጡ ህዝቡ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጎን ሆኖ ማገዝ ይኖርበታል፡፡ዶከተር ሙሉ አያይዘውም፤ “የትግራይን ህዝብ ከምትናገረው ስትሰማው ብዙ ትምህርት ትወስዳለህ። እኛ እየሠራን ነው፤ የቀረውን ህዝቡ ሊያግዘን ይገባል። ህዝባችን ያለንን ልንሰማ፣ ራሱ የፈለገውንም ሊመርጥ ይገባል” ሲሉ ለተወያዮቹ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38160
[ { "passage": "በትግራይ ክልልና በፌደራል መንግሥት መካከል አየተካሄደ ባለው ግጭት ውስጥ የኤርትራ መንግሥት በቀጥታ ተሳታፊ ሆኗል ሲሉ የትግራይ ርዕሰ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ተናገሩ።የኤርትራና የኢትዮጵያ መንግሥታት ግን በትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት በኩል የቀረበውን ክስ ሐሰት ነው ሲሉ አጣጥለውታል። ፕሬዚዳንቱ በዛሬው ዕለት ህዳር 1/2013 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ የኤርትራ ሠራዊት አባላት በምዕራብ ትግራይ በኩል ከፍተኛ ድብደባ ፈፅመዋል ሲሉ ከሰዋል።\"በትናንትናው ዕለት የኤርትራ ሠራዊት አባላት ከፌደራል መንግሥት ጋር በመወገን በሁመራ በካባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ፈፅመዋል\" ብለዋል።ከዚህም በተጨማሪ የኤርትራ ሠራዊት አባላት በዛሬው ዕለት ድንበር ጥሰው በባድመ በኩል በመግባት ጦርነት ከፍተዋልም ሲሉ በመግለጫቸው ላይ ያከሉት ደብረፅዮን የኤርትራ መንግሥት በጦርነቱ ተሳታፊ መሆን፣ ጦርነቱን \"ወደተለየ ምዕራፍ አሸጋግሮታል\" ብለዋል።።\"አሁንም ተመልሰን ወደዚህ ጦርነት መግባታችን ያሳዝናል። ባለፈው ይብቃ- ብለን ነበር። ወደ ሌላ ምዕራፍ ተሸጋግረናል። ትግራይ ላይ ትልቅ ክህደት ተፈጽሞባታል\" ብለዋል።\"ኤርትራውያን ይሄ ሁኔታ እንዳይፈጠር ብዙ ጥረት አድርጋችኋል። አመስግነናል። አሁንም እናመሰግናለን። ይሁን እንጂ ኢሳይያስ ከዐብይና ከአሃዳዊ ኃይሎች ጋር በመወገን የጀመርነውን ራሳችንን የመከላከል ዘመቻ ሊያከሽፍ መጥቷል። ይህንን ያደረገው በጦርነቱ የኛን የበላይነት አይቶ ነው\" በማለትም ተናግረዋል።ይሁን እንጂ በጦርነቱ የኤርትራ ሠራዊት አባልት በቀጥታ ተሳትፈዋል ስለመባሉ ቢቢሲ ከገለልተኛ አካል ማረጋገጥ አልቻለም።ሆኖም የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ ይህንን የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንትን ክስ ማጣጣላቸውን ሮይተርስ በዘገባው አመልክቷል።\"ይሄ ውስጣዊ ግጭት ነው። እና የግጭቱ አካል አይደለንም\" ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በስልክ እንደገለጹለት ሮይተርስ ዘግቧል።በተመሳሳይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ተሰማ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደተናገሩት በኤርትራ ወታደሮች ጥቃት ስለመፈጸሙ በደብረጺዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) የተሰጠው መግለጫ \"ፍፁም ሐሰት\" መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ አቅጣጫዎች ዘመቻ እያካሄደ የሚገኘው የፌደራል መንግሥት ሠራዊት በምዕራብ የሚገኘውን የሁመራ አየር ማረፊያን መቆጣጠሩን የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዛሬ [ማክሰኞ] ጠዋት ዘግበዋል። ከዚህም በተጨማሪም በአካባቢው የነበሩ የትግራይ ልዩ ኃይል፣ ፖሊስ እና ሚሊሻ አባላትም እጃቸውን ሰጥተዋል ብለዋል።ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሻከረ የመጣው የፌደራልና የትግራይ ክልል መንግሥት ግንኙነት የማይታረቅ ደረጃ ደርሶ ከሳምንት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የትግራይ ልዩ ኃይል በክልሉ የሚገኘውን የመከላከያ ሰሜን ዕዝ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልፀው ጦርነት መከፈቱን አስታውቀዋል።ጠቅላይ ሚንስትሩ በአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው የመከላከያ ሠራዊት በኮማንድ ፖስት እየተመራ \"አገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል\" ብለዋል።የትግራይ ክልል በበኩሉ በክልሉ የሚገኙት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰሜን ዕዝ ሰራዊት አባላትና አዛዦች ከትግራይ ክልል መንግሥት ጎን ለመሰለፍ ወስነዋል ማለቱ ይታወሳል። ", "passage_id": "2746eac481992bec70c89b793fd074c6" }, { "passage": "የትግራይ ህዝብ ያምናቸው የነበሩ አመራሮች ላይ ጥርጣሬ እንዲኖረውና እንዲፈራቸው ማድረጉን የህወሓት ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ ፡፡በመቐለ ከተማ ከጥር 3 ጀምሮ እየተካሄደ ባለው 7ኛው የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ግምገማ አስመልክተው አቶ ጌታቸው ረዳ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የትግራይ ህዝብ እንዲፈራ አመራሩ ማድረጉ በፍፁም ተቀባይነት የሌላውና ለግል ጥቅም ሲባል የተደረገ መሆኑን አመልክተዋል ።\n\n\n\n\nበክልሉ በተለይም አገሪቱ ስጋት ላይ እንድትወደቅ ባደረጉ አመራሮችና አሰራሮች ላይ ለውጥ እንደሚደረግም ነው ያመለከቱት።በመቐለ ከተማ 2ሺህ 500 የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችና የአባል ድርጅቶች ተወካዮች እየተሳተፉ አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን አቶ ጌታቸው ገልጸዋል ፡፡", "passage_id": "7ee28a737b9561e6d89717b64f0beb82" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የህወሓት ጁንታ በትግራይ ክልል ባሉ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ የነበሩ የህግ ታራሚዎችን ሰብስቦ በመቐለ ከተማ ውስጥ በመልቀቅ ዝርፊያ እንዲፈጸም ማድረጉን የከተማዋ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አታክልቲ ኃይለስላሴ ገለፁ፡፡በመንግሥት የተወሰደውን የህግ ማስከበር ዕርምጃ ተከትሎ የጁንታው አባላት በክልሉ የተለያዩ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ በተለያዩ ወንጀሎች ተይዘው የእስር ጊዜያቸውን እየፈጸሙ የነበሩ ታራሚዎችን መቐለ ከተማ ለቀዋቸዋል። በዚህም በከተማዋ ውስጥ የዝርፊያ ወንጀል እንዲፈጽሙና ህዝቡ በስጋት ውስጥ እንዲወድቅ አድርገዋል ብለዋል አቶ አታክልቲ።በበርካታ ወንጀሎች ተይዘው የነበሩ ሰዎችን በከተማዋ ውስጥ በመልቀቅ የግለሰቦች ሱቅ ጭምር እንዲዘረፉ ተደርጓልም ነው ያሉት፡፡ይህን ያደረጉት አንድም ተቋማትን በመዝረፍ ሰነዶችን ለማጥፋት፣ ሁለትም ሕዝቡ ወደ ስጋት እንዲገባና እንዲጠራጠር በማድረግ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በአዲሱ አስተዳደር ላይ እምነት እንዲያጣ ለማድረግ መሆኑንም አስረድተዋል።በዚህም ብዙ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ሆን ተብለው እንዲዘረፉ ተደርጓል ብለዋል አቶ አታክልቲ ኃይለስላሴ፡፡በከተማዋ የታየው ዝርፊያ በጁንታው ትዕዛዝ የተፈጸመ መሆኑን በመግለጽም፤ በተለይ በዋና ዋና መስሪያ ቤቶች ላይ ራሳቸው እዚያ ይሠሩ የነበሩ ሰዎች አንዳንድ ሰነዶችን ያጠፉበት መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህ ረገድ የከተማ አስተዳደሩ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ሙሉ ለሙሉ መዘረፉን ተናግረዋል።በተጨማሪም የሕዝብ አገልግሎት መስጫዎች የሆኑት የፍትህ ተቋማት፣ ማዘጋጃ ቤት፣ ፍርድ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ሰነዶች ተዘርፈዋል ያሉት አቶ አታክልቲ፥ በእነዚህ ተቋማት ውስጥ ሆን ተብሎ የተቀናጀ ዝርፊያ ከተፈጸመ በኋላ ተሰርቆ ነው ለማለት ተቋማቱን ክፍት አድርገው መተዋቸውንም አስረድተዋል። ይህንን አጋጣሚ የተጠቀሙ ሌሎች ዘራፊዎችም የተለያዩ ቁሳቁሶችን መዝረፋቸውንም ጠቁመዋል።አሁን ከተማዋ ወደ ዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዋ እየተመለሰች መሆኗን የሚያሳዩ ጥሩ እንቅስቃሴዎች አሉ ያሉት አቶ አታክልቲ፤ ህብረተሰቡን ያማከለ ሥራ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመሆን እየተሠራ ስለሆነ በአጭር ቀናት ውስጥ መቐለ ወደነበረችበት መደበኛ እንቅስቃሴ እንደምትመለስ አረጋግጠዋል።ለዚህም በከተማ ደረጃ በምናቋቁመው ምክር ቤት ሕዝቡ በቀጥታ የሚመርጣቸው የየትኛውም ፖለቲካ ፓርቲዎች አባል የሆኑና ለውጡን ደግፈው ሕዝቡን ወደ ተሻለ ደረጃ ሊያሸጋግሩ የሚችሉ አካላት ወደኃላፊነት ይመጣሉ ብለዋል፡፡አሁን የተፈጠረውን ጊዜያዊ ምስቅልቅል በመቆጣጠርና በመምራት ኃላፊነት ወስደው የሚሠሩ፣ ሕዝቡም የተቀበላቸው እና ጥሩ ስነምግባር ኖሯቸው በሕብረተሰቡ አካባቢ ያለውንና የሚነሱትን የፍትህ፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በፍቃደኝነት መሥራት የሚችሉ ሰዎች በሙሉ የሚካተቱበት ዕድል እንዳለ መናገራቸውን ኢፕድ ዘግቧል፡፡", "passage_id": "ee162d4efc999be4c6a59d414b51419a" }, { "passage": "ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) በትግራይ ላይ የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ በተቋረጠው ድምፂ ወያነ ትግራይ የፌስቡክ ገፅ በድምፅ ባስተላለፉት መልዕከት ክልሉ ላይ ደርሷል ስለተባሉ ውድመቶች፣ ቀጥሏል ስላሉት የትግል ሁኔታ እንዲሁም ለትግራይ ህዝብና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ያሉትን ጥሪ አስተላልፈዋል።\n\nመንግሥት በበኩሉ ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል ያቀረቧቸው ክሶች \"መሰረተ የሌላቸው\" እና ዓላማቸውም \"የህወሓትን አጸያፊ ወንጀሎች ለመሸፋፈን ነው\" ይላል። \n\nከአሜሪካ እየተላለፈ እንደሆነ በተገለፀው የድምፂ ወያነ ገጽ ላይ የተሰራጨው ድምጽ በትክክልም የደብረጺዮን (ዶ/ር) ስለመሆኑ እና መቼ እንደተቀረፀ ቢቢሲ ከገለልተኛ ወገን ማጣራት አልቻለም።\n\nደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) በትግራይ ላይ የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭት አስመልክቶ \"ህዝቡ ራሱን በራሱን የማስተዳደር መብቱን በተግባር ለማረጋገጥ በፅናት ስለታገለ የተቃጣበት ጦርነት\" ያሉት ሲሆን አራት መንግሥታትና የክልሎች ልዩ ኃይሎች ተሳትፈውበታል ብለዋል።\n\nአራቱ ብለው የጠሯቸው መንግሥታት እነማን እንደሆነ ባይዘረዝሩም \"በዚህም ምክንያት የኃይል አለመመጣጠን አጋጥሟል\" በማለት አስረድተዋል። \n\nበተለያዩ ሪፖርቶች የኤርትራ ወታደሮች መሳተፋቸው የተጠቀሰ ሲሆን በቅርቡ የኤርትራ ወታደሮች ከትግራይ ክልል በአስቸኳይ እንዲወጡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) መጠየቁ ይታወሳል።\n\nየኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ በተደጋጋሚ ይህ ህግ የማስከበር ዘመቻ እንደሆነና በትግራዩ ግጭት የኤርትራ ጦር አለመሳተፉን ማሳወቁ የሚታወስ ነው።\n\nየፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት በኅዳር ወር አጋማሽ ላይ መቀለን ከተቆጣጠረ በኋላ በትግራይ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ መጠናቀቁን መግለጹ ይታወሳል።\n\nመቀለ በፌደራል መንግሥቱ ሰራዊት በቁጥጥር ሥር ከዋለች በኋላ የህወሃት ሊቀ መንበር ለሮይተርስ ትግሉ እንደሚቀጥልና \"ትግሉ የራስን መብት በራስ የመወሰን እንደሆነ\" ገልጸው ነበር።\n\nበፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የእስር ትዕዛዝ የወጣባቸው ደብረ ፅዮን ገ/ሚካኤል በአሁኑ ወቅት የት እንዳሉ በግልጽ ባይታወቅም የአገሪቱ የመከላከያ አዛዦች ግን ተፈላጊዎቹ የህውሓት አመራሮች በትግራይ ተራራማ ቦታዎች ተደብቀው እንደሚገኙ ሲገልጹ ተሰምተዋል። \n\nለእስር ማዘዣው ዋነኛ ምክንያቶቹ በትግራይ ክልል በሚገኘው በአገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈፀም፣ የአገር ክህደት ወንጀል በመፈፀም፣ የመከላከያ ሠራዊትና የፖሊስ አባላት እንዲታገቱ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው ነው።\n\nደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል በጠቀሱት ትግል \"ከፍተኛ ዋጋ ጠይቋል\" ያሉ ሲሆን። \"የህወሃት መስራች አባላት ከሚባሉት ላለፉት 45 ዓመታት ከያዙት ህዝባዊ መስመር ፈቀቅ ሳይሉ የታገሉና የመሩ፣ ያታገሉና ብዙ ድል ያስመዘገቡ አዛውንት ነባር ታጋዮች በዚህ የወረራ ጦርነት፣ በጠላት እጅ ተጎድተውብናል። ከባድ መስዋዕትነት ከፍለዋል። አሁንም እየከፈሉ ይገኛሉ። የነዚህ ጀግኖቻችን መስዋዕትነት የበለጠ ቁጭትና እልህ ያስንቀናል እንጂ ፈፅሞ ከትግላችን የሚያቆመን አይሆንም።\" ብለዋል\n\nዶ/ር ደብረፅዮን መስዋዕት ሆነዋል ያሏቸውን ግለሰቦች በስም ባይጠቅሱም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና አምባሳደር የነበሩት አቶ ስዩም መስፍን፣ በተለያዩ የሥልጣን ቦታ ላይ የነበሩት አቶ አባይ ጸሐዬ፣ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ አስመላሽ ወልደሥላሴ እንዲሁም ከመከላከያ ሠራዊቱ ከድተዋል የተባሉት ኮሎኔል ኪሮስ ሐጎስ በግጭቱ ወቅት እጅ አልሰጥም በማለታቸው መገደላቸው ተነግሯል።\n\nበትግራይ ክልል ደርሷል ስለተባለው ውድመት\n\nደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል በክልሉ ላይ ደረሱ ስላሏቸው ጥቃቶችና ዘርፈ ብዙ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች... ", "passage_id": "555f21edb6f9a209b538b04f5ea52d32" }, { "passage": "የትግራይ ክልልና የፌደራል መንግሥት ወታደራዊ ግጭት ውስጥ ከገቡ ሶስተኛ ቀናቸውን አስቆጥረዋል። ግጭቱን ተከትሎ በመቀሌ ከተማና በክልሉ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክና የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀምሯል።የኤሌክትሪክ አገልግሎት ትናንት ጥቅምት 26/2013 ዓ.ም የተመለሰ ሲሆን የትራንስፖርት አገልግሎት ደግሞ በዛሬው ዕለት ጥቅምት 27/2013 ዓ.ም መጀመሩን የመቀሌ የቢቢሲ ዘጋቢ ገልጿል።ምንም እንኳን ትራንስፖርት ቢጀመርም ከመቀሌ ከተማ ወደተለያዩ ክፍሎች የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች በሙሉ ከከተማው ፖሊስ ልዩ ፍቃድ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል።ግጭቱን ተከትሎ የተቋረጠው የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት አሁንም እንደተቋረጠ ነው።ከቀናት በፊት ተኩስ የተሰማባት የመቀሌ ከተማ በአንፃራዊ ሁኔታ የተረጋጋ ሁኔታ ላይ ብትገኝም ማህበረሰቡ ግን ጦርነቱ በፈጠረው ውጅንብር ስጋት ላይ መሆኑንም የቢቢሲ ዘጋቢ ይናገራል።በትናንትናው እለት በመቀሌ ከተማ የጦር አውሮፕላን ሲያንዣብብ የነበረ መሆኑን የታዘበው የቢቢሲ ዘጋቢ በድምፁም በርካቶች መደናገጥና ፍራቻ ውስጥ እንደገቡ አክሎ ገልጿል። በዛሬው ዕለት ነዋሪው የእለት ተእለት ኑሮውን የተመለሰ ይመስላል።በከተማዋ ውስጥ ያሉ ባንኮችም ዝግ ሲሆኑ ነዋሪው ከትናንት በተሻለ ሁኔታ ከተማዋ ውስጥ እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ታዝቧል።ከዚህም በተጨማሪ መቀሌ የሚገኙ የንግድ ተቋማትና የገበያ ማዕከላትም አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ብሏል።የአማራን ክልል በሚያዋስነው የምዕራብ ትግራይ ድንበር በኩል ግጭቶች እንዳሉና ውጊያው መቀጠሉን የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) በትናንትናው ዕለት ገልፀዋል።የአማራ ልዩ ኃይልና የፌደራል ሰራዊቱ በጥምረት በመሆን የትግራይ ኃይል ጋር መዋጋታቸውን ተናግረዋል።በዛሬውም እለት በምዕራብ ትግራይ በኩል ጦርነቱ የቀጠለ መሆኑ መረጃዎች የወጡ ቢሆንም የፌደራል መንግሥቱም ሆነ የትግራይ ክልል ዝርዝር መረጃዎችን ከመስጠት ተቆጥበዋል።በአሁኑ ወቅት ወቅት በከተማዋ አንዳንድ የነዳጅ ማደያ ጣብያዎች አገልግሎት እየሰጡ ቢሆንም በከተማዋ የቤንዚን እጥረት መኖሩም ተገልጿል።የመማር ማስተማር ሂደቱን ለመታዘብ የሞከረው የቢቢሲ ዘጋቢ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት የስምንተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እንዲወስዱ የሚጠብቁ ተማሪዎች በአፄ ዮሃንስ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ቀጥለዋል።ግጭቱ ከመጀመሩ በፊት በትምህርት ገበታቸው ላይ የነበሩት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ግን ትምህርታቸው እንደተቋረጠም ዘጋቢያችን ያገኘው መረጃ ያስረዳል።ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሻከረ የመጣው የፌደራልና የትግራይ ክልል መንግሥት ግንኙነት የማይታረቅ ደረጃ ደርሶ ከቀናት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ህወሃት በትግራይ የሚገኘው የመከላካያ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልፀው ጦርነት መከፈቱን አስታውቀዋል።ጠቅላይ ሚንስትሩ በአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው የመከላከያ ሠራዊት በኮማንድ ፖስት እየተመራ \"ሀገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትእዛዝ ተሰጥቶታል\" ብለዋል።የትግራይ ክልል በበኩሉ በክልሉ የሚገኙት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰሜን ዕዝ ሰራዊት አባላትና አዛዦች ከትግራይ ክልል መንግሥት ጎን ለመሰለፍ ወስነዋል ብሏል። ", "passage_id": "0f2c5f619b89ff6c611a4f3cee7ef757" } ]
cfd0d75d32e93d4b6de5fed2b1b5f4a0
55c0f335dae61d69a53becfa7c83027f
ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የ100 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ተፈራረሙ
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የ100 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ የብድር ስምምነቱን በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ያስሚን ወሀብሬቢ እና በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ኤርትራ ዳይሬክተር ኦስማን ዲዮን ተፈርሟል።በስምምነቱ ወቅት ሚኒስትር ዴታዋ ያስሚን እንደተናገሩት፤ ከዓለም ባንክ የተገኘው የ100 ሚሊዮን ዶላር የብድር በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ የተሰማሩ ሴት ሥራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍና አዳዲስ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ያግዛል። ገንዘቡም በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ የተሰማሩ ሴት ሥራ ፈጣሪዎች የክህሎት ስልጠና አግኝተው ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል።አበዳሪ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትንና ጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ ቢሮዎች የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ እንደሚረዳቸው የጠቆሙት ሚንስትር ዴኤታዋ፤ የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ የምታደርገውን የልማት ሥራ ለመደገፍ ለሰጠው የፈጣን ምላሽም አመስግነዋል።በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ኤርትራ ዳይሬክተር ኦስማን ዲዮን በበኩላቸው፤ ብድሩ በአነስተኛና ጥቃቅን ዘርፍ የተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን ሴቶችን ለማገዝ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የተደረገው የብድር ስምምነትም በአነስተኛና ጥቃቅን ዘርፍ የተሰማሩ ሴቶች ክህሎታቸውን በማሳደግ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል፣ አዳዲስ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ገቢን ለማሳደግ እንደሚስችላቸው ገልፀዋል።የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ ሥራ ፈጣሪ ሴቶችና ወጣቶችን ለማበረታታት የምታደርገውን ጥረት ለማገዝ የሚያደርገው ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም የተናገሩት ዳይሬክተሩ፤ የብድር ስምምነቱ ከ38 ሺህ በላይ ሴት ሥራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ የሚውል መሆኑንም አንስተዋል። የሚገኘው ገንዘብ በአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ መቀሌ፣ አክሱም፣ ባህር-ዳር፣ ጎንደር፣ ሐዋሳ፣ ዲላ፣ አዳማ፣ አሰላ እና በመላ አገሪቱ በሚገኙ ሌሎች 89 የሥራ ዕድል መፍጠሪያ ማዕከላት (ሳተላይቶች) ተግባራዊ እንደሚሆኑ የተገለፀ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ የገንዘብ እጥረት ያለባቸውን ጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅቶች ብድር የሚያገኙበትን መንገድ ለማመቻቸት ብሎም ኮቪድ-19 በሥራቸው ላይ ጫና ያሳደረባቸውን ሴቶች ለመደገፍ እንደሚያግዝ ተነግሯል።በአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሚሆኑ ሥራ ፈጣሪ ሴቶችም ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ከፍተኛ ማስያዣ ብድር ለማግኘት እንደሚያስችላቸው፤ እንዲሁም በአነስተኛና ጥቃቅን ዘርፍ የተሰማሩ ሴት ሥራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ የካናዳ፣ ጣሊያን፣ የጃፓን መንግሥትና እና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እገዛ ሲያደርጉ የቆዩ መሆኑን እና ወደ ፊትም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ስለመነገሩ የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38170
[ { "passage": "የመጀመሪያው ስምምነት ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ለተመረጡ የኢትዮጵያ ባንኮች በዓለም አቀፍ የንግድ ፋይናንስ መርኃ ግብር አማካይነት ድጋፍ የሚያደርግበት ሲሆን ሁለተኛው ስምምነት ደግሞ ኮርፖሬሽኑ ለኢትዮጵያ በብር ብድር የሚያቀርብበት ነው ተብሏል።\n\n\"የዛሬው ስምምነት ኢትዮጵያ ለግሉ ዘርፍ ዕድገት ያላትን ቁርጠኛነት ይጠቁማል\" ሲሉ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የተናገሩት የፋይናንስ እና የኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ናቸው።አቶ አህመድ ጨምረውም መንግሥት የፋይናንስ ዘርፉን ለማሳደግ ከፖሊሲ ምርመራ አንስቶ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የብሄራዊ ባንክ ገዥ ይናገር ደሴ በበኩላቸው ስምምነቶቹ ኢትዮጵያ ላጋጠማት የውጭ ምንዛሬ እጥረት ችግር የመፍትሄ አካል ከመሆኑም በላይ ለግሉ ዘርፍ ፋይናንስ በማቅረብ ረገድ ከፍ ያለ ሚና አለው ብለዋል።\n\n• ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ በቅዳሜው ውይይት ላይ ምን አሉ? \n\n• ከአፋር እስከ ዲሲ፤ በዚህ ሳምንት የሚጠበቁ ክስተቶች\n\n• ቁርስ የቀኑ እጅግ አስፈላጊ ምግብ ነውን?\n\nለግሉ ዘርፍ የፋይናንስ ምንጩን ማብዛት አለብን፤ ይህ የዚህ ስምምነት አንደኛው አካል ነው\" ብለዋል ገዥው።ከዚህም በተጨማሪ \"የግሉን ዘርፍ ባካተተ ሁኔታ የካፒታል ገበያ በኢትዮጵያ አውድ እንዴት ሊሠራ እንደሚችል ጥናት እያካሄድን ነው\" ሲሉ የባንኩ ገዥ አክለው ተናግረዋል።ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (አይኤፍሲ) በዓለም ባንክ ሥር የግሉን ዘርፍ የሚመለከት ክንፍ ሆኖ የተቋቋመው እ.ኤ.አ በ1950ዎቹ አጋማሽ ሲሆን በማደግ ላይ ባሉ አገራት የግሉን ዘርፍ ዕድገት የማበረታትን ሥራ ይከውናል። አይኤፍሲ አባል ሆነው በመሠረቱት አገራት ባለቤትነት የተያዘ እና የሚተዳደር ተቋም ነው። \n\nፈረንሳይዊው ፍሊፕ ለ ዌሩ እ.ኤ.አ ከመጋቢት 2016 አንስቶ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።ሥራ አስኪያጁ በኢትዮጵያ የስድስት ቀናት ቆይታቸው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር የተገናኙ ሲሆን የሃዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክንም ጎብኝተዋል። ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎች ጋር በነበራቸው ቆይታ የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ እርስ በእርስ እንዲተማመኑ እንደሚያስፈልግ መናገራቸውን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ፍፁም አረጋ በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ ጠቅሰዋል። \n\nኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የንግድ ሥራ ክንውን የሚያቀላጥፉ የማሻሻያ እርምጃዎችን ለመውሰድ በኮሚሽኑ እና በኮርፖሬሽኑ መካከል የትብብር ስምምነት ላይ መደረሱንም አቶ ፍፁም አክለው ገልፀዋል።ሥራ አስጂያጁ በልጅነታቸው ወቅት አዲስ አበባ በሚገኘው የሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ተከተታትለው የነበረ ሲሆን በቆይታችው ወቅት ትምህርት ቤቱን እንደጎበኙ ዛሬ ሰኞ ቀትር ላይ ለጋዜጠኞች ባደረጉት ገለፃ ተናግረዋል።\n\nየኢትዮጵያ ባንኮች ከተለያዩ የዓለም አገራት ባንኮች ጋር የብድር ስራን በሚያከናውኑበት ወቅቅ በቂ የሆነ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ካልተገኘ በስራው ላይ ችግሮች እንደሚፈጠሩ ያስረዱት የብሄራዊ ባንክ ገዥ ይናገር ደሴ፤ የዛሬው ስምምነት አይኤፍሲ ዋስትና እንደሚሰጥ የሚያረጋግጥ በመሆኑ፤ ይህም የኢትዮጵያ ባንኮች ከውጭ አገራት አቻዎቻቸው ጋር ያላቸውን ስራ የሚያቀል ነው ብለዋል። \"ሲጠቃለሉ ሁለቱ ስምምነቶች ተጨማሪ ዶላር ላገሪቱ ያስገኛሉ፤ ለግሉ ዘርፍ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ያመጣል፤ ላገጠመን የውጭ ምንዛሬ ችግር ዋስትና ይሰጣል\" ሲሉ ተናግረዋል።\n\n ", "passage_id": "f41f1eea238c28fe15862d275876aa44" }, { "passage": "የዓለም ባንክ በቅርቡ ይፋ ያደረገውን የኢትዮጵያ የአጋርነት ማዕቀፍ የድጋፍ ሰነድን በማስመልከት ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀው፣ በኢትዮጵያ የ13 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ባላቸው ፕሮጀክቶች አማካይነት ለአገሪቱ ድጋፍ እያደረገ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ዳይሬክተር ካሮሊን ተርክ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳስታወቁት፣ ባንኩ በአገሪቱ ድጋፍ በሚሰጥባቸው ፕሮጀክቶች አማካይነት የሚመዘገቡት ውጤቶች ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገሮች ይልቅ የባንኩን ድጋፍ በማግኘት ቀዳሚ እንድትሆን አብቅተዋታል፡፡ በአገሪቱ ለሚታዩት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጦች አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ፕሮግራሞችን በቴክኒክና በፋይናንስ እየደገፈ የሚገኘው የዓለም ባንክ፣ ለመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሚተገበረውን የአጋርነት ማዕቀፍ ሰነድ ከቀናት በፊት ይፋ ማድረጉ አይነዘጋም፡፡ ይህንኑ በማስመልከት ዳይሬክተሯ በሰጡት ማብራሪያ፣ ባንኩ ድጋፍ እያደረገባቸው ከሚገኙት ሥራዎች መካከል ለመጪዎቹ ሦስት ዓመታት የሚውለው አምስት ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋው የፋይናንስ ድጋፍ ይጠቀሳል፡፡ በአገሪቱ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ እንዲመጣ በዚህም የትምህርት ዘርፉ እንዲስፋፋ፣ የገጠርና የከተማ ምርታማነት እንዲጨምር፣ ወጣቶች ሥራ እንዲያገኙ የሚያስችሉ ሥራዎች ላይ የሚያተኩረው የአጋርነት ማዕቀፉ አንዱ ተልዕኮ ነው፡፡ አሳታፊና ለቀውሶች የማይገበር የኢኮኖሚ አቅም እንዲፈጠር ማገዝ በሚለው የባንኩ የአጋርነት ማዕቀፍ ውስጥ ከሚካቱት ውስጥ፣ የሴፍቲኔት ፕሮግራም ይጠቀሳል፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ማብራሪያ በኢትዮጵያ ከ14 ሚሊዮን ያላነሱ ሰዎች ለምግብ ዋስትና ችግሮች በመዳረጋቸው፣ ባንኩ ለዕለት ደራሽ ዕርዳታዎች እንዲሁም ለሴፍቲኔት ፕሮግራሞች ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህም ሆኖ በአገሪቱ በየጊዜው የድህነት መጠን እየቀነሰ ቢመጣም፣ ከድርቅና ከምርታማት መቀነስ ጋር በሚያያዙ በምግብ ዋስትና ችግሮች ሳቢያ የሚያጋጥመው ፈታኝ ሁኔታ ባንኩ ከሚጠቅሳቸው ችግሮች መካከል ይመደባሉ፡፡ የሕፃናት መቀንጨርና የተመጣጠነ ምግብ ማጣትም የአገሪቱ መሠረታዊ ችግሮች ከሚባሉት ውስጥ ይመደባል፡፡ የጤና፣ የትምህርት ሽፋን፣ የውኃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን አገልግሎቶችን ጨምሮ በርካታ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በአዲሱ የአጋርነት ማዕቀፍ ትኩረት ከተሰጣቸው መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ እንዲህ ያሉ ግቦችን ለማሳካት ባንኩ መንግሥትን ተጠያቂ የሚያደርጉና የሙስና ወንጀሎች ላይ ትኩረት የሚያደርጉ አሠራሮችንም እንደሚከተል ይፋ አድርጓል፡፡ መንግሥት የሚተገብራቸውን ፕሮጀክቶች ለሕዝብ ይፋ በማድረግ ግልጽነትና ተጠያቂነትን እንዲያሰፍን ባንኩ የሚንቀሳቀስባቸውን ማዕቀፎች እንዳከተተ የገለጹት ካሮሊን ተርክ፣ ከዚህ ቀደም በባንኩ ድጋፍ በአገሪቱ ሲተገበር በቆየውና በመንደር ማሰባሰብ በሚባለው ፕሮጀክት አማካይነት ስለደረሰው ችግርም ሪፖርተር ጥያቄ አቅርቦላቸው አብራርተዋል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2012 በባንኩ ፀድቆ የ600 ሚሊዮን ዶላር ፋይናንስ የተለቀቀለትና የመሠረታዊ አገልግሎት ማስፋፊያ ፕሮጀክት (Promoting Basic Services) ምዕራፍ ሦስት ትግበራ ፕሮግራም፣ በመንግሥትና በባንኩ ላይ ተቃውሞን አስከትሎ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ በአኙዋ ጎሳ አባላት አማካይነት ለባንኩ የኢንስፔክሽን ቡድን የቀረበውን ጥሪ መነሻ በማድረግ በተካሄደ ምርመራ፣ የጋምቤላ ክልል መንግሥት 45 ሺሕ አባወራዎችን በመንደር የማሰባሰብ ዕቅድ ነበረው፡፡ ይህም በክልሉ ከሚገኙ አባወራዎች ውስጥ 70 በመቶ ያህሉን የሚሸፍን ዕቅድ እንደነበር አጣሪው ቡድን ከሦስት ዓመት በፊት ይፋ ባደረገው የምርመራ ሪፖርት ጠቅሶታል፡፡ ከክልሉ ዕቅድ ውስጥ 37,883 ወይም 60 በመቶው አባወራዎች በአንድ መንደር እንዲሰባሰቡ መደረጉንም የአጣሪው ቡድን ሪፖርት አመላክቷል፡፡ ይህ በመሆኑም ባንኩ ለማኅበራዊና አካባቢያዊ ተፅዕኖዎች የተቀመጠውን የጥበቃ መሥፈርት አላከበረም ተብሎ ተተችቷል፡፡ የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድም ስለጉዳዩ ምላሽ እንዲሰጥ አስገድዶት ነበር፡፡ እንዲህ ያሉ ስህተቶች እንዳያጋጥሙ ባንኩ እየሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ዳይሬክተሯ፣ ከዚህ ሪፖርት ውጪ እስካሁን በአካባቢና በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የባንኩን አቋም በሚጣረሱ ፕሮጀክቶች ውስጥ አለመሳተፉን ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በኋላም ቢሆን ባንኩ ለሚደግፋቸው ፕሮጀክቶች አስፈላጊውን ግምገማ እያደረገ የሚስከትሉት አካባቢያዊና ማኅበራዊ ጉዳት እየተፈተሸ ፕሮጀክቶችን እንደሚያፀድቅ አብራርተዋል፡፡  የመንግሥትን አቅም ለመገንባት ረጅም ጊዜ በመውሰዱ ምክንያት የተፈጠረ ክፍተት እንደነበረም ጠቁመዋል፡፡ ይህም ሆኖ ኢትዮጵያ የባንኩን ድጋፍ በማግኘት በአፍሪካ ቀዳሚ እንደሆነች ያብራሩት ዳይሬክተሯና የሥራ አጋሮቻቸው፣ ቃል በተገባውም ሆነ ባንኩ በለቀቃቸው የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ ረገድ ኢትዮጵያ የተሻለ ውጤት እያሳየች እንደምትገኝ ገልጸዋል፡፡ ባለው ዓመት የ1.3 ቢሊዮን ዶላር ብድር መልቀቁን የባንኩ ኃላፊዎች ጠቁመው፣ በዚህ ዓመትም 1.2 ቢሊዮን ዶላር እንደሚለቀቅ ገልጸዋል፡፡ኢትዮጵያ በአማካይ በየዓመቱ ቃል ከተገባው ውስጥ ከ39 እስከ 42 በመቶ የሚሆነው ገንዘብ እየተለቀቀላት እንደምትገኝ ያስታወቁት ካሮሊን፣ ለመጪዎቹ ሦስት ዓመታት የሚውል የአምስት ቢሊዮን ዶላር አዲስ የፋይናንስ ማዕቀፍ በመምጣቱ፣ በጠቅላላው የ13 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው ፕሮጀክቶች በባንኩ ድጋፍ እየተደረጋላቸው ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ላለፉት አምስት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የአጋርነት ስትራቴጂ ሰባት ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የገንዘብ ድጋፍ እንደነበረው የባንኩ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ", "passage_id": "c055a934d15b6bfbb9231427e302341d" }, { "passage": "የግሉን ክፍለ-ኢኮኖሚ የመዋዕለ-ነዋይ አቅም ሊያግዝና ሊገነባ የሚያስችል የተባለ ስምምነት ዓለምቀፍ የገንዘብ ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ጋር ተፈራርሟል።ኮርፖሬሽኑ የሃገሪቱ የልማት እንቅስቃሴ ስትራተጂያዊ አጋር ለመሆን መወሰኑን ኃላፊው ገልፀዋል።ዛሬ የተፈረመው ስምምነት መንግሥት የግሉን ክፍለ-ኢኮኖሚ ለማሳደግ ያለውን ቁርጠኛነት ያሳያል ተብሏል። ", "passage_id": "665c76a546319df20f70d070b170c9d7" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ እና የሳዑዲ አረቢያ የልማት ፈንድ የ140 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የብድር ስምምነት በዛሬው እለት ተፈራርመዋል።የብድር ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና የሳዑዲ አረቢያ የልማት ፈንድ ምክትል ሊቀ መንበር ካሊድ አልክሁድራ ናቸው የተፈራረሙት።ብድሩም በአነስተኛ ወለድ በረጅም ጊዜ የሚከፈል መሆኑም ተገልጿል።ከብድር ስምምነቱ 75 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላሩ ከደብረ ማርቆስ- ሞጣ ለሚገነባው የመንገድ ፕሮጀክት የሚውል ሲሆን፥ የመንገድ ፕሮጀክቱም 118 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ነው።የስምምነቱ ሁለተኛ አካል የሆነው 65 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ደግሞ ለዋን ዋሽ ብሄራዊ ፕሮግራም የሚውል መሆኑም ነው የተገለፀው።በአላዛር ታደለ", "passage_id": "5fefaf934f715c2a1c96b9e9a7ffde23" }, { "passage": "የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ 2 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍና ብድር ማጽደቁን አስታወቀ ።  ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ትናንት ባካሄደው ስብሰባ በአጠቃላይ 1ነጥብ2  ቢሊዮን ዶላር  ድጋፍና ብድሩን  ማጽደቁን  ገልጿል።ባንኩ እንደገለጸው 600 ሚሊየን ዶላሩ በድጋፍ መልክ የሚሠጥ ሲሆን፥ 600 ሚሊየን ዶላሩ ደግሞ ብድር ነው።ባንኩ ድጋፍና ብድሩን  ለመሥጠት  ያቀደው የኢትዮጵያ መንግስት ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ መሆኑን አስታውቋል።የኢትዮጵያ መንግስት የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ማድረጉን እንዲሁም የፖለቲካ ምህደሩን ማስፋቱ ቀጠናዊ መረጋጋት እንዲመጣ የበኩሉን ጥረት እያደረገ መሆኑንም ለድጋፉ ትልቅ አስተዋጽኦ  ማድረጉ ተጠቅሷል። ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ መንግስት የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማሻሻዎች ማድረጉን እና ይህ ጥረቱም እንዲሳካ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ  ነው  ባንኩ እንደዚህ አይነት ምላሽ  መሥጠቱም ተመልክቷል። ባንኩ ያደረገው የገንዘብ ድጋፉና ብድሩ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፏን እና የኢንቨስትመንት ምህዳሯ ላይ ማሻሻያ እንድታደርግ  የሚረዳ መሆኑን ተጠቅሷል  ። (ምንጭ: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር) ", "passage_id": "6bd58e91251f3dbed4c5d49d93e33107" } ]
2eea43a1d7107df1ab3fad08d87d4742
acb120ea2706d44a947613b1253582e0
ከመተከል ዞን ቡለን ወረዳ የተፈናቀሉ ወገኖች ለረሃብ አደጋ መጋለጣቸውን ተናገሩ
መሀመድ ሁሴን አዲስ አበባ፡- በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በሚገኙ ቀበሌዎች በንፁሃን ላይ ከተፈፀመው ጥቃት አምልጠው በቡለን ከተማ የተጠለሉ ተፈናቃዮች በረሃብና በጥም የተነሳ ለሞት አደጋ መጋለጣቸውን ተናገሩ፡፡ አስተያየታቸውን ትናንት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ የሰጡት እነዚሁ ተፈናቃዮች፤ ከግድያው ለማምለጥ ምንም ነገር ሳይዙ ከቤታቸው በመውጣታቸው የተነሳ አሁን ላይ የሚበሉትና የሚጠጡት እንዳጡና ከመንግሥትም ያገኙት ድጋፍ እንደሌለ በምሬት ተናግረዋል። የስምንት ልጆች አባት የሆኑትና በበኩጂ ቀበሌ ከአስር ዓመታት በላይ የኖሩት አርሶ አደር ደረጀ በየነ እንደገለፁት፤ ከሞት አምልጠውና ከአርባ አምስት ኪሎ ሜትር በላይ በእግራቸው ተጉዘው ቡለን ወረዳ መድረስ ቢችሉም፣ በርሃብና በጥም የተነሳ ሌላ ሞት እንደተጋፈጡና ጠያቂ የመንግሥት አካል እስካሁን አላገኙም። በወረዳው ሥር የሚገኙ ሁሉም የቀበሌ ነዋሪዎች የእግር መርገጫ እስኪጠፋ ድረስ በቡለን ወረዳ ተሰባስበው በረሃብ እየተቆሉ ይገኛሉ ያሉት አርሶ አደር ደረጀ፤ ‹‹ህይወታቸውን ካጡት እህት ወንድሞቻችን ሐዘንና ድንጋጤ ሳንወጣ ይዘን የሸሸናቸውን ልጆቻችንን ልናጣ የምንችልበት አደገኛ የረሃብ ችግር ውስጥ ወድቀናል፡፡ ጠያቂ አካል አላገኘንም፡፡ ትምህርት ቤቶች እና አዳራሾች በተፈናቃዮች ሞልተው ተጨናንቀዋል፡፡ ህፃናት ልጆቻችን የሚልሱት የሚቀምሱት አጥተዋል፡፡ በዚህ የተነሳም በከፍተኛ ጭንቀት ላይ እንገኛለን›› ሲሉ ሀሳባቸውን በምሬት ገልፀዋል፡፡ ‹‹በፍራቻና በሥጋት ሰቀቀን ውስጥ መኖር ከጀመርን ዓመት አልፎናል፡፡ ከወረዳና ከክልል የሚመጡ አመራሮች የጉሙዝ ማህበረሰብን ብቻ ለይተው ይሰበስባሉ፡፡ ለእኛ ዞረው ሰላም ነው፤ ምንም ችግር አይደርስባችሁም እያሉ ሲያዘናጉን ኖረዋል፡፡ ስለዚህ ከጀርባ ሌላ የጭፍጨፋ ሴራ እየተዘጋጀ ሕዝቡ እንዳይነቃ እና ወደሌላ አካባቢ እንዳይሸሽ ሲደረግ ኖሯል፡፡ በዚህ የተነሳም ከበኩጂ ብቻ ያለቀው ሰው ብዙ ነው፡፡ እኔ በዓይኔ ተሰብስቦ የተመለከትኩት 207 አስከሬን ነው” ያሉት አርሶ አደር ደረጀ፤ የወንድማቸው አምስት ልጆችና ባልና ሚስትን ጨምሮ ሰባት ቤተሰባቸው እንደተገደሉባቸው በሐዘን ተናግረዋል፡፡ የጭላንቆ ቀበሌ ነዋሪው የሆኑት ሌላው አስተያየት ሰጪ አርሶ አደር ወንድማገኝ ሻምበል በበኩላቸው፤ የተፈፀመው ዘግናኝ ጭፍጨፋ አስከፊ ከመሆኑም በላይ በህይወት የተረፍነውም ለከፍተኛ መከራ ዳርጎናል ብለዋል፡፡ “ህፃናት እና ሴቶች ከጭፍጨፋው አምልጠው በቡለን ወረዳ በመሰባሰብ በከፍተኛ ረሃብ ላይ ወድቀዋል፡፡ ማንም የሚጠይቅ አካል የለም፡፡ በዚህ የተነሳ ከፍተኛ ተጨማሪ እልቂት መፈጠሩ አይቀርም” ሲሉ አርሶአደሩ ሥጋታቸውን አስረድተዋል፡፡ አመራሩ የችግሩ ዋና አካል መሆኑን ያነሱት አርሶ አደር ወንድም አገኝ ፤ ‹‹ከወረዳ ወደ ቀበሌ የሚመጡ አመራሮች እኛን ሊያስገድሉን ነበር፡፡ ከጭላንቆ ቀበሌ ሩጠን በማምለጥ ከምሽቱ ሦስት ሰዓት አዲስ ዓለም ከምትባል ቀበሌ ገብተን ተቀመጡ መከላከያ ሠራዊት መጥቶላችኋል ብለው አታለሉን። በዚህም የተነሳ ወንድማችን በአራት ቀስት ተመትቶ ሞቷል›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ሕብረተሰቡ አብሮ ከጉምዝ ብሔረሰቦች ጋር ቡና የሚጠጣ ሕዝብ ነው ያሉት አርሶ አደሩ፤ “ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እኛ ወደ ማሣ ሥራ ስንሄድ ከወረዳ ከሚመጡ አመራሮች ጋር ብቻቸውን ይመክራሉ፤ በዚህም የተነሳ ጥቃቱ እየጨመረ መጥቷል›› ብለዋል፡፡ “ብዙ ወገኖቻችንን በግድያው ከማጣታችን በላይ በመከራ ላይ መከራ፣ በችግር ላይ ችግር እያሰቃየን እንገኛለን፡፡ የሦስት ቀን አራስ ህፃን ልጅ በዘንቢል ይዘን ነው የወጣነው፡፡ አዝመራዬን ወቅቼ 180 ኩንታል ሜዳ ላይ እንደደረደርኩት ትቼው ወጥቻለሁ፡፡ መኪና እንኳን ማግኘት አልቻልንም፡፡ አምልጠን የወጣነውም በእግራችን ነው፡፡ ባዶ ራቁታችንን ወጥተን ቡለን ብንደርስም ሌላ መከራ ነው የጠበቀን፡፡ ወድቀን ያለነው ከሕብረተሰቡ ላይ ነው፡፡ እኔ አመራር ነኝ ብሎ ተፈናቃዮችን ያነጋገረና የጠየቀ አካል እስካሁን የለም›› በማለት ብሶታቸውን ተናግረዋል፡፡ በጉሙዝ ማህበረሰብ እና በሌላው ሕብረተሰብ መካከል ምንም አይነት ችግር እንደሌለ የገለፁት አስተያየት ሰጪዎቹ፤ “የሚያስፈጁን በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ኃላፊነት የተሰጣቸው አመራሮች እኩይ ድርጊት በመሆኑ አጥርቶ እርምጃ መውሰድ እና የተፈናቀለውን ማቋቋም አስፈላጊ ነው” ሲሉ መፍትሄ ያሉትን ጠቁመዋል፡፡ እንደ ዝግጅት ክፍል የነዋሪዎቹን አስተያየት በመያዝ ወደሚመለከታቸው የቤንሻንጉል ክልል የሥራ ኃላፊዎች በመደወል ጉዳዩን ለማጣራትና አስተያየታቸውን እንዲሰጡን ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ ሆኖም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ለኢቢሲ በሰጡት አስተያየት፤ በግድያው እጃቸው አለበት ተብለው የሚጠረጠሩት አመራርም ይሁን፣ ግለሰቦችም ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ እርምጃ እየወሰዱ መሆናቸውን አስታውቀዋል። “አሁንም ቢሆን በህብረተሰቡ በተለያዩ አጋጣሚዎች በተደጋጋሚ በግጭቱ ላይ የአመራሮች ተሳትፎ አለበት የሚል ነገር አለ፡፡ እኛ ዝግ አላደረግነውም፤ እንደክልል መንግሥት የሚወራው ወሬ እንደተጠበቀ ሆኖ የማጥራት ሥራዎች በመሥራት ተጨባጭ ማስረጃዎች ስናገኝ ማንኛውም ሰው ወደ ሕግ እንዲቀርብ እያደረግን ነው ያለነው” ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ። አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38181
[ { "passage": "የመተከል ዞን ተፈናቃዮች በቻግኒ። የመተከል ዞን ባለፉት ሶስት አመታት የተለያዩ ጥቃቶችን ያስተናገደ ሲሆን በተለይም ከመስከረም 2013 ጀምሮ ተደጋጋሚ ማንነነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶችን በዞኑ ተፈጽመዋል።\n\nየተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እንዳለው ባለፈው አንድ ወር ውስጥ ብቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከምዕራባዊው የኢትዮጵያ ከፍል የመተከል ዞን ተፈናቅለው ወደ ጎረቤት ሱዳን መሸሻቸውን ገልጿል። \n\nየኤጀንሲው ቃል አቀባይ ብባር ባሌክ ትናንት በጄኔቫ በሰጡት መግለጫ ላይ እንደገለፁት፤ ከኢትዮጵያ ወጥተው ወደ ሱዳኗ የብሉ ናይል ግዛት የገቡት ሰዎች ቁጥር 7 ሺህ ይደርሳል ተብሎ ይገመታል።\n\nእስካሁን 3 ሺህ የሚሆኑትን መመዝገብ መቻሉን ጠቅሰው፤ በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ ተፈናቅለው የመጡ ሰዎችን መመዝገብ ሲቻል ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችል የኤጀንሲው ቃል አባይ ተናግረዋል።\n\nባለፉት ሳምንታት ውስጥ ብቻ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ከሌሎች አጋሮቹ ጋር በመሆን ወደ 1 ሺህ ለሚጠጉ ተፈናቃዮች እርዳታ አቅርቧል ያሉት ቃል አቀባዩ፤ ድጋፉ ምግብ፣ ህክምና፣ ውሃ እና የንፅህና መጠበቂያዎችን እንዲሁም ሌሎች የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦቶችን ያጠቃለለ ነው ሲሉ ገልፀዋል። \n\nቀሪዎቹን ጥገኝነት ጠያቂዎች የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ ሱዳናዊያን ተቀብለው እያስተናገዷቸው እንደሚገኙ ተገልጿል። \n\nበቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመተከል ዞን ባለፉት ሦስት ዓመታት የተለያዩ ጥቃቶች በነዋሪዎች ላይ ተፈጽሞ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን በተለይም ከመስከረም 2013 ጀምሮ ተደጋጋሚ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ተከስተዋል። \n\nበተለይ በአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ውስጥ በሚገኘው የመተከል ዞን የአማራ፣ የኦሮሞ እንዲሁም የሺናሻ ተወላጅ የሆኑ ነዋሪዎች ላይ በተፈጸሙ ተደጋጋሚ ጥቃቶች ተከፍተኛ ቁጥር ያለው ሞትና መፈናቀል ማጋጠሙ ይታወቃል። \n\nበዚህም ሳቢያ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ የግድያ፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመት እንዲሁም የማፈናቀል ተግባራት ተደጋግመው እንደተፈጸሙ የአገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች በተደጋጋሚ ገልፀዋል።\n\nበአሁኑ ጊዜ የክልሉና የፌደራል መንግሥት በጋራ ያወቀሩት የዕዝ ማዕከል ተደጋጋሚ ችግር ባጋጠመባቸው አካባቢዎች ሠላምና መረጋጋት ለማስፈን የእርዳታና የመልሶ ማቋቋም ተግባራትን እያከናወኑ መሆኑ መገለጹ ይታወሳል። \n\nየክልሉ ፖሊስ ከፌደራል የጸጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ጥቃት ፈጽመዋል በተባሉ ኃይሎች ላይ እርምጃ መውሰዱን የአገር ውስጥ መገናና ብዙሃን ከዚህ በፊት የዘገቡ ሲሆን፤ በመተከል ዞን ከተፈጠረው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ እጃቸው አለበት የተባሉና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ አልተወጡም የተባሉ አመራሮችን በሕግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው መገለጹ አይዘነጋም። \n\n ", "passage_id": "2cade442d0c4a1884948457714b31ea8" }, { "passage": "በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር በመፍራት የሰብዓዊ ድጋፍ ለማጓጓዝ ለሰጉ የተሽከርካሪ ባለንብረቶች የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ።በክልሉ አንድ መቶ ሺህ የሚጠጋ ተፈናቃይ መኖሩንና ከመንግሥትም ሆነ ከረጂ ድርጅቶች ድጋፍ እየተገኘ ቢሆንም በአካባቢው በአለው የፀጥታ ስጋት ምክንያት ከፌደራልም ሆነ በክልሉ ውስጥ ወደ ተለያዪ አካባቢዋች እህል ለማድረስ አለመቻሉን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ገልጿል።ተፈናቃዪቹ ባሉበት ከተማ የሚገኙ ነዋሪዋች ቤታቸውን ለቀው ከ15 እስከ 20 ድረስ በቤታቸው እያስተናገዱ መሆኑን ተፈናቃዪቹ አመስግነዋል።\n", "passage_id": "7e628893448afbb2a9c5145dff881705" }, { "passage": "በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ራንች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች የመድኃኒት ድጋፍ እንዲቀርብ ጠየቁ፡፡ባሕር ዳር፡ ታኅሥሥ 21/2013 ዓ.ም (አብመድ) ከመተከል ዞን ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ራንች መጠለያ ጣቢያ የሰፈሩ ተፈናቃዮች ከመንግሥት የጤና ተቋማት የማያገኙትን መድኃኒት በግል ገዝተው ለመጠቀም ባለመቻላቸው መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡ወይዘሮ ጦቢያው ጓንጉል ከመተከል ዞን ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ራንች በተባለ ጊዜያዊ መጠለያ ይገኛሉ፡፡ ወይዘሮ ጦቢያው የስኳር ህመም ታማሚ በመሆናቸው ወደ ጤና ጣቢያ ሄደው በነፃ ሙሉ የምርመራ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ምርመራውን አጠናቀው እንደወጡ መድኃኒት በጤና ተቋም ማግኘት ባለመቻላቸው ከግል ገዝተው እንዳይጠቀሙ የተፈናቀሉት ባዶ እጃቸውን በመሆኑ በሐኪም የታዘዘላቸውን መድኃኒት አለመውሰዳቸው ለጤና ችግር መዳረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ወይዘሮ ጦቢያው በመጠለያ ጣቢያው የመድኃኒት አቅርቦት አለመኖሩ ሞት እዚህም ተከትሎአቸው እንደመጣ ያህል እየተሰማቸው ነው። በመንግሥት የጤና ተቋማት ከምርመራ አገልግሎት በተጨማሪ መድኃኒት ሊቀርብላቸው እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡የተፈናቃዮች የጤና ኮሚቴ ሆነው በጊዜያዊነት በተቋቋመው መጠለያ በመሥራት ላይ የሚገኙት አቶ መለሰ ደሳለው ለተፈናቃዮች ጤና ትኩረት እየተሰጠ አለመሆኑን ነግረውናል። በሚኖሩበት አካባቢ በቂ መጸዳጃ፣ መጠለያ፣ ምግብ እና ውሃ የሌለ በመሆኑ የጤና ችግር እየገጠማቸው እንደሚገኝም ተናግረዋል።ከ50 ሰው በላይ በአንድ ድንኳን እንደሚገኝ የገለጹት አቶ መለሰ                                                                        ይህም ለተላላፊ በሽታዎች እንዳይጋለጡ ስጋት እንደፈጠረባቸው                                                                          ገልጸዋል።                                                                      መንግሥት ሁኔታዎች ተለውጠው ወደ ቀዬአቸው እስኪመለሱ                                                                           ትኩረት በመስጠት አስፈላጊ የህክምና እና የመድኃኒት ድጋፍ                                                                             እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ያነጋገርናቸው ሐኪም መኮንን ምናየሁ (ዶክተር) ዜጎች ከሚደርስባቸው ግድያ ለመሸሽ ከቀያቸው ሲፈናቀሉ በቅድሚያ ምግብ፣ ውሃ፣ መጠለያ፣ መጸዳጃ እና የህክምና አገልግሎት በፍጥነት ካላገኙ ለተለያዩ የጤና እክሎች ይዳረጋሉ ብለዋል፡፡ ኮሌራ፣ተቅማጥ፣ ወባ፣ ኮሮና ወረርሽኝ፣ የስኳር በሽታ፣ የደም ግፊት፣ ሳንባ ነቀርሳ፣ ድብርት እና ሌሎችም የተፈናቃዮች ስጋት ናቸዉ ብለዋል።መንግሥት እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የምግብ፣ የውሃ፣ የመጸዳጃ ቤት እና የጤና አቅርቦት ቅድሚያ ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል። ተፈናቃዮች በተጨናነቀ መጠለያ መኖራቸውን የተመለከቱት ዶክተር መኮንን መንግሥት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማቅረብ እና እንዲሁም የአስቸኳይ ጊዜ የህክምና ቡድን ማቋቋም እንደሚገባው ተናግረዋል።የቻግኒ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አቶ ያሬድ ስማቸው ዜጎች ከመተከል ዞን ተፈናቅለው ከመጡበት ቀን ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ጤና ጣቢያዎች እና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከጤና መምሪያ፣ ከጤና ቢሮ እና ከጤና ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡በቅርቡ ደግሞ የድንገተኛ አደጋ መከላከል እና መቆጣጠር ባለሙያ ተመድቦ ነፍሰጡር፣ የሚያጠቡ እናቶችን እና የምግብ እጥረት ያለባቸውን ሕጻናት የተለየ ድጋፍ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ኀላፊው አስታውቀዋል። ተከታታይ መድኃኒት የሚወስዱ፣ መድኃኒት ጀምረው ያቋረጡ ተፈናቃዮች ለተጨማሪ ህመም እንዳይጋለጡ የወረዳው ጤና ጥበቃ እየሠራ ነው ብለዋል።ለ927 ተፈናቃዮች እስከ አሁን የህክምና አግልግሎት መስጠታቸውን የተናገሩት አቶ ያሬድ የሆስፒታል እና የጤና ጣቢያ ባለሙያዎች ተናበው እንዲሰሩ መደረጉንም አስረድተዋል።ከጤና ሚኒስቴር እና ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመሆን ተንቀሳቃሽ ክሊኒክ ተቋቋሞ ተፈናቃዮች ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲታከሙ እየተመቻቸ እንደሆነም ነግረውናል፡፡ከብሔረሰብ አስተዳደሩ አንድ አምቡላንስ ለተፈናቃዮች ብቻ በመመደብ አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ለሚፈልጉት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ኀላፊው ተናግረዋል፡፡ተፈናቃዮች ከሆስፒታል ያላገኙትን መድኃኒት ከጤና ጣቢያ እንዲያገኙ ይደረጋል ያሉት የጤና ጥበቃ ጽሕፈት ኀላፊው በአሁኑ ወቅት በቂ የመድኃኒት አቅርቦት ባለመኖሩ ለተፈናቃይ ታማሚዎች በቂ መድኃኒት ማቅረብ አልተቻለም ብለዋል። የክልሉ ጤና ቢሮም ክትትል የሚያደርጉ ባለሙያዎችን ወደ ሥፍራው እንደተላከ ታውቋል።", "passage_id": "2d007405930552709e5fc60ed16f11ef" }, { "passage": "ዘንድሮ የጣለው ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ ከ22 ሺህ በላይ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን የአማራ ክልል መንግሥት አስታወቀ። በጣና ዙሪያ ያሉ የጎርፍ ሰለባዎችም መንግሥት የሰብዓዊ ድጋፍ አላደረገልንም እያሉ ነው።የአማራ ክልል መንግሥት በበኩሉ ከአሰራር ክፍተት ካልሆነ በስተቀር አስፈላጊው ድጋፍ ወደ የአካባቢዎች ተልኳል ብላል።።\n", "passage_id": "6d9b7f989ecd19230efcaebef2111d4d" }, { "passage": "ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደቡብና ሰሜን ወሎ ዞኖች የሰፈሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች አሰፋፈራችን ለኮሮናቫይረስ ተጋላጭ ሊያደርገን ይችላል ሲሉ ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡\nየሁለቱም ዞኖች አመራሮች አቅም በፈቀደ ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ተናግረዋል፡፡\n", "passage_id": "257a84ae1c5664c0b6b380bd50db40e7" } ]
1d2e502eb68809b27e7408458ef69f51
6b07adb188e128bd441e9ee7b40d557e
በትግራይ ክልል ያሉ ኢንዱስትሪዎችን ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ
ፋንታነሽ ክንዴአዲስ አበባ፡-ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ሥራ ለማስጀመር እየሠራ መሆኑን አስታወቀ። በክልሉ ከተሰማሩ ባለሀብቶች ጋርም ውይይት አድርጓል።የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዮሐንስ ድንቃየሁ በትግራይ ክልል ከተሰማሩ ባለሀብቶች ጋር ትናንት ውይይት ባካሄዱበት ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ያሉበት ደረጃ እየተጣራ ሲሆን፤ ወደ ሥራ እንዲገቡ ለማድረግም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በትግራይ ክልል በተወሰደው ሕግ ማስከበር እርምጃ ወቅት የተጎዱ ኢንዱስትሪዎች ካሉ በትክክለኛ መረጃ ላይ በመመስረት ተገቢውን ድጋፍ አግኝተው በተቻለ ፍጥነት ወደሥራ እንዲመለሱ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህንንም ተከትሎ በኢንዱስትሪዎች ላይ የደረሰውን ችግርና የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ የሚያጠና ቡድን በሚኒስቴሩ መቋቋሙን አስታውቀዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙ ባለሀብቶችም በሕግ ማስከበሩ ምክንያት ፋብሪካቸው ላይ የደረሰውን ጉዳትና ከመንግሥት የሚፈልጉትን ድጋፍ አቅርበዋል። በወቅቱ እንደገለጹትም፤ የፋብሪካዎችና ማምረቻ መሣሪያዎች ውድመት፣ ለሠራተኛ ደመወዝ ለመክፈል መቸገር፣ የወደብ ኪራይ፣ ምርት ለማቅረብ ውል ፈጽመው በወቅቱ ማቅረብ አለመቻል፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ ከጉምሩክና ባንክ ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች በባለሀብቶቹ ከተነሱት ችግሮች መካከል ናቸው። አንዳንድ ባለሀብቶች በደረሰባቸው ከፍተኛ ውድመት ምክንያት መንግስት ከፍ ያለ ድጋፍ ካላደረገላቸው ወደ ሥራ ለመመለስ እንደሚቸገሩ ሲገልጹ፤ ሌሎች ደግሞ በፋብሪካቸው ላይ የከፋ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው በመግለጽ የተወሰነ እገዛ ካገኙ በአጭር ጊዜ ሥራ እንደሚጀምሩ ተናግረዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ እንዳሉት፤ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በአጭር ጊዜ፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ሊፈቱ የሚችሉ ችግሮችን እየለዩ በፍጥነት እየፈታ ይሄዳል። ባለሀብቶችም ትክክለኛ መረጃ በመስጠት የሚያስፈልጋቸውን እገዛ እንዲጠይቁ አሳስበዋል። ከወደብ፣ ከመሰረተ ልማትና ከጉምሩክ ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ጥያቄዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያየት አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ አብራርተዋል።በቅርቡ ሥራ መጀመር የሚችሉና የውጭ ምንዛሬ ችግር ያለባቸው ባለሀብቶች የውጭ ምንዛሬ እንዲያገኙ በብሔራዊ ባንክ መፈቀዱን በመግለጽም፤ ሥራ ማስኬጃ የሚፈልጉ ካሉም ተገቢው ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ተናግረዋል። ኢንዱስትሪዎችም ሠራተኞችን ሳይበትኑ በተቻለ ፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገቡ ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38172
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ታህሳስ 12፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ እና በዙሪያው ባሉ ከተሞች ተቋርጦ የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ወደ መደበኛ አገልግሎት አሰጣጡ ሙሉ በሙሉ ለመመለስ እየተሰራ እንዲያገኝ ተገለጸ። በአሁኑ ወቅት ዋጃ፣ አላማጣ፣ ኮረም፣ ማይጨው፣ መሆኒ፣ ዓዲጎሱ፣ አዲ ጉደም፣ ኩሓ፣ መቐለ፣ ውቅሮ፣ አጉላዕ፣ ዓዲግራት፣ ሓውዜን፣ አጉላዕ እና በአፋር ክልል የሚገኘው በርሃሌ ከተማም ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡በተጨማሪም ፍረወይኒ፣ ዕዳጋ ሐሙስ፣ ዓብይ አዲ፣ ዛላንበሳ፣ ደውሃን፣ የጭላ፣ ሀገረ ሠላም እና አፅቢ በቅርብ ቀን ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ እየተሰራ ይገኛል፡፡የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮች በትግራይ ክልል በአንዳንድ ቦታዎች በመዘዋወር የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ላይ ምልከታ አካሂደዋል።ቡድኑ እስከ ታህሳስ 12 ቀን 2013 ዓ.ም የመስክ ምልከታ ያደረገባቸው የመቀሌ፣ ኩሂያ፣ ውቅሮ፣ አጉላ፣ ፍረወይኒ፣ እዳጋሀሙስ፣ ነጃሺ፣ አዲግራት ከተሞች የሚገኙ የአገልግሎቱ ሠራተኞችና ቢሮዎችን እንዲሁም በጥገና ስራ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችን ጭምር በመጎብኘት ከማበረታታቱ ባሻገር ያጋጠሟቸውን ተግዳሮቶች የለየ ሲሆን በቀጣይ ሊደረጉ የሚገባቸው ድጋፎችንም ለይቷል፡፡ሠራተኛው በክልሉ በተፈጠረው ሁኔታ በመሠረተ ልማቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ቢሆንም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅንጅት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ህብረተሰቡ የተቋረጠበትን ኤሌክትሪክ እንዲያገኝ ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ መሆኑ በአካል በተደረገ የመስክ ምልከታ ለማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን ጉዳት የደረሰበትን መስመር መልሶ በመጠገን ወደ ስራ ለማስገባት ተቋሙ ባለ 50 ኤሲ 45ሺህ ሜትር፣ ባለ 95 ኤሲ 9 ሺህ እና ኮምፖስድ ኢንሱሌተር የተባሉ ግብዓቶች ለክልሉ እንዲደርስ የተደረገ ቢሆንም ኔትዎርኩ ላይ ከደረሰው ጉዳት አኳያ በቀጣይ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል፡፡ በመጨረሻም ስለ ነባራዊ ሁኔታና ቀጣይ አቅጣጫ ዙሪያ በመቀሌ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመገኘት ከማኔጅመንቱ ጋር የምክክር መድረክ በማድረግ ጉብኝቱን አጠናቋል፡፡የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት በአፋጣኝ ወደ ቀድሞው አገልግሎት ለመመለስ ሲሰሩ የቆዩ የትግራይ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ክፍል ሰራተኛች የማኔጅመንት አባላት አድንቀዋል፡፡ተቋሙ በክልሉ ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ጠግኖ ሁሉንም የክልሉ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ እንደሚሰራ አስታውቋል፡፡", "passage_id": "2d8a4ae0202ac81fcea46cf62d819031" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ በክልሉ የኃይል መቋረጥ ያጋጠመው ማክሰኞ የካቲት 09/2013 ዓ. ም ከሰዓት በኋላ ጀምሮ ነው።\n\nበመላው አገሪቱ ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚያስተዳድረው ተቋሙ እንዳለው \"የጁንታው ርዝራዦች\" ያላቸው በክልሉ ባለ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በፈፀሙት ጥቃት በመላው ትግራይ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት መቋረጡን ገልጿል። \n\nየተጠቀሱት ኃይሎች አዲጉዶም ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ከአላማጣ - መሆኒ - መቀለ በተዘረጋ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በፈጸሙት ጥቃት በክልሉ ኤሌክትሪክ መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ገልጿል። \n\nየትግራይ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከሚያገኝባቸው መስመሮች አንዱ የሆነውና ጥቃት የተፈጸመበት የአላማጣ - መሆኒ - መለለ መስመር ሲሆን ሌላኛው የተከዜ አክሱም መስመር ደግሞ የጥገና ሥራው እየተከናወነ እንደነበር ድርጅቱ ገልጿል። \n\n\"የተቆረጠው ማስተላለፊያ መስመር ነው። ይህ ነው ኃይል እንዲቋረጥ ያደረገው። ጉዳቱ ይሄ ብቻ ከሆነ በአጭር ጊዜ ውስጥ ያልቃል። ሌሎች ጉዳቶች ደርሰው ከሆነ ግን መስመሮቹን መፈተሽ ያስፈልጋል\" ብለዋል አቶ ሞገስ።\n\nበደረሰበት ጥቃት ለኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆነው ይህ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት የነበረ ሲሆን ለመጠገንም ረዘም ያለ ጊዜ እንደወሰደ ተቋሙ አመልክቷል። \n\nበጥቅምት ወር መጨራሻ ላይ በትግራይ ክልል የተቀሰቀሰውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በደረሰ ጉዳት ለረዥም ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ የነበረ ሲሆን በክልሉ ያሉ የተለያዩ አካባቢዎች ኃይል መልሰው ለማግኘት ረዘም ላለ ጊዜ ለመጠበቅ ተገደው ቆይተው ነበር። \n\nበትግራይ ክልል ውስጥ በተዘረጉ ኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት መሠረተ ልማቶች ላይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ሳቢያ ሕዝቡ ከኃይል አቅርቦት ውጪ ከመሆኑ ባሻገር በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ የወጣባቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች መውደማቸው መገለጹ ይታወሳል። \n\nየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደረሰባቸው ጥቃት ከአገልግሎት ውጪ የሆኑትን ለትግራይ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቀርብባቸውን መሠረተ ልማቶች በመጠገን የክልሉ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲመለስ እየሠራ መሆኑን ገልጿል። \n\nየትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትናንትናው ዕለት፣ ማክሰኞ፣ በትግራይ ክልል ቴሌቪዥን ላይ ባስተላለፈው መግለጫ ክልሉ እንዳይረጋጋ ለማድረግ የሚሞክሩ \"የተበተኑ የህወሓት ኃይሎች\" እንዳሉና ሕዝቡም ለእነዚህ ኃይሎች መጠጊያ እንዳይሰጥ ማሳሰቡ ይታወቃል። \n\nጊዜያዊው አስተዳደር በመግለጫው \"የተበተኑ\" ያላቸው የህወሓት ኃይሎች በሕዝቡ ውስጥ መሸሸጋቸውን አመልክቶ \"የጥፋት ኃይሎች በመንደሮችና በከተሞች ውስጥ ተሰማርተው የሕዝቡን ሠላም በማናጋት ወደ ሌላ የከፋ ቀውስ እንዲገባ እየሠሩ ነው\" ብሏል። \n\nጨምሮም በእነዚህ ኃይሎች ላይ ሊወሰድ በሚችለው እርምጃ ሕዝቡ እንዳይጎዳ \"የጥፋት ኃይሎቹን አሳልፎ እንዲሰጥ ወይም ለደኅንነቱ ሲል ራሱን ከእነዚህ ኃይሎች እንዲያርቅ\" አሳስቧል። \n\nበጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ በትግራይ ክልል የተቀሰቀሰውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ የፌደራል መንግሥት በወሰደው ወታደራዊ እርምጃ የክልሉ አስተዳዳሪ የነበረው የህወሓት አመራሮች ከስልጣን በማስወገድ ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም መደረጉ ይታወሳል። \n\nወታደራዊ ግጭቱን ተከትሎ በክልሉ የኤሌክትሪክ ኃይል በመቋረጡ ምክንያት የውሃ፣ የባንክ፣ የስልክ፣ የኢንተርኔትና ሌሎች መሠረታዊ አገልግሎቶች ለረዥም ጊዜ ተቋርጠው ቆይተው አብዛኛው የክልሉ... ", "passage_id": "d212856d5c4c727490d63dbe5c34bdf5" }, { "passage": "በአማራ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ለ920ሺ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ የቴክኒክ፣ሙያና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ገለፀ፡፡በተለይም ዕድገት ተኮር ዘርፍ በሆኑትና ቅድሚያ በሚሰጣቸው በማኑፋክቸሪንግና በኮንስትራክሽን ዘርፍ ለሚሰማሩ ወጣቶች የተለየ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ የቢሮው ኃላፊ አቶ ጌታቸው ጀምበር ለዋልታ ተናግረዋል፡፡በከተማ ግብርና ዘርፍ ለሚሰማሩ ወጣቶችም ተገቢው ድጋፍና ትብብር እንደሚደረግ ነው ኃላፊው የተናገሩት፡፡ የሥራ ዕድል ፈጠራው የማምረቻና የመሸጫ ቦታዎችን እንደሚያካትትም አቶ ጌታቸው ጠቁመዋል፡፡  በ2008 ዓ.ም ለ905ሺ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ 835ሺ ያህሉን ለማሳካት መቻሉን አቶ ጌታቸው አስረድተዋል፡፡ ለእነዚህም ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦትም ተመቻቶላቸዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተገኙትን ጠንካራ ጎኖች በማጠናከር ለተሻለ ለውጥ እንደሚሰራም ነው የተናገሩት፡፡ለማህበራቱ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ በየከተሞቹ እንደሚቀርቡ አቶ ጌታቸው ጠቁመው የብድር አቅርቦትም በመንግስት በኩል እየተመቻቸላቸው ነው ብለዋል፡፡ በራሳቸው ካፒታል መንቀሳቀስ ለሚፈልጉ አካላትም የመስሪያና የመሸጫ ቦታ እንደሚመቻችላቸው አስገንዝበዋል፡፡የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ለሚያገኙት ሙያዊና የቴክኒክ ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ወጣቶች በማህበር ተደራጅተው የሥራ ፈጣሪነት ባህልን አዳብረውና አጎልብተው ራሳቸውን፣ቤተሰባቸውንና አገራቸውን እንዲጠቅሙ ቢሮው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እየሰራ እንደሚገኝ ተመልክቷል፡፡በዘርፉ ለሚሰማሩ አካላትም በአገር ውስጥና በውጭ የገበያ ትስስር ይፈጠርላቸዋል፡፡ ለዚህም በተለያዩ ማህበራት መካከል ፣በወረዳና በአገር ዓቀፍ ደረጃ እንዲተሳሰሩ የማድረግ አካሄድ እንደሚተገበር ነው ያስረዱት፡፡ ማህበራቱ በተለያዩ ጊዜና ቦታ በሚዘጋጁ ባዛሮችና ኤግዚብሽኖች ላይ በመሳተፍ ምርታቸውን በማስተዋወቅና በመሸጥ የገበያ ትስስራቸውን እንዲያጠናክሩ ይደረጋል፡፡የተሻለ ሀብት ያፈሩ አካላትም ወደ መካከለኛ ኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲሸጋገሩ እየተደረገ መሆኑን ከቢሮው ገለፃ ለመረዳት ተችሏል፡፡", "passage_id": "85fc47683af2ea8da71c5d329ef6251f" }, { "passage": "የመቐለና ኮምቦልቻ ኢንዱስትሪፓርኮች ሙሉ በሙሉ በባለሃብቶች መያዛቸውን የኢንዱስትሪ  ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ ።  የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሲሳይ ገመቹ ከዋልታ ቴሌቭዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት የመቐለና የኮምቦልቻ ኢንደስትሪ ፓርኮች የመሥሪያና የማምረቻ  ቦታዎች ሙሉ በሙሉ በባለሃብቶች የተያዙ መሆናቸውን ገልጸዋል ።በሁለቱም የኢንዱስትሪ ፓርኮች ባለሃብቶቹ ተጨማሪ የመሥሪያ ቦታ እየጠየቁ እና እየተመቻቸላቸው እንደሆነ ሥራ አስፈጻሚው  ጠቁመዋል ፡፡መንግሥት ሼዶችን ከመገንባት ውጪ የለማ መሬት በማዘጋጀት በመቐለና ኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለባለሃብቶች እያቀረበ መሆኑንና ባለሃብቶችም በተሠጣቸው የለማ መሬት የራሳቸውን የማምረቻ ቦታ ግንባታ እንዲከናውኑ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩላቸው መሆኑን አያይዘው ገልጸዋል ።  በተጨማሪም ግንባታቸው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙት የድሬዳዋ ፣የአዳማ ፣የጅማ ፣የቦሌ ለሚ ሁለትና የቂሊንጦ ኢንደስትሪ ፓርኮች በቀጣይ ሶስት ወራት ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ ከፍተኛ ጥረት  እየተደረገ እንደሆነም ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል፡፡", "passage_id": "6f9d94476f32f55c6963b75b6797e9f2" }, { "passage": "ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ የስልክ አገልግሎት የተቋረጠው ከትናንትና ማምሻ ጀምሮ መሆኑን ገልፀው ወደ ሥፍራው ባለሙያዎችን መላካቸውንና የጥገና ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል።\n\nየፋይበር መቋረጡ ያጋጠመው በመቀሌ እና አዲሽሁ ከተማ መካከል የሚገኝ መሆኑን ገለልፀው፣ በአሁኑ ሰዓት በመቀሌ እንዲሁም ሌሎች አቅራብያ አካባቢዎች ያሉ ቡድኖች ገብተው ጥገና እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል።\n\n\"በአሁኑ ሰዓት ሶስት ቡድን በጥገናው ላይ ተሰማርቷል\" ያሉት ኃላፊዋ በትግራይ ክልል በደረሰው ውድመት የተጎዱ የስልክ መስመሮች ላይ በሚካሄደው ጥገና \"ፕሮቴክሽን እና ሪስቶሬሸን ሲስተም ላይ ያሉት በሙሉ ተጠግነው ባለማለቃቸው\" አሁን ይህ ጉዳት ሲደርስ በፍጥነት ማገናኘት አለመቻሉን አስታውቀዋል።\n\nፋይበሩ የተቆረጠው በተፈጥሮ ምክንያት አልያም ሆን ተብሎ በሰው መሆኑን ገና አለማወቃቸውን የገለፁት ኃላፊዋ በቦታው የሚገኘው የባለሙያዎች ቡድን ጥገና እያካሄደ መሆኑን ጨምረው አክለዋል።\n\nበመቀሌ ከተማ ከትናንት ማምሻውን ጀምሮ የስልክ አገልግሎት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን የድርጅቱ ኃላፊ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት ዛሬ ረቡዕ በሰዓታት ውስጥ ጥገና ተደርጎ ይመለሳል ብለዋል።\n\nበትግራይ ክልል የሕወሓት ኃይሎች በሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መክፈታቸው ከተገለፀ በኋላ መንግሥት \"የሕግ የማስከበር\" እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጦ መቆየቱ ይታወሳል።\n\nከሁለት ወራት በፊት በክልሉ በተከሰተው ወታደራዊ ግጭት ሳቢያ ተቋርጠው የነበሩት የመብራት፣ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎቶች በከፊል የተመለሱባቸው አካባቢዎች ቢኖሩም፤ በበርካታ ከተሞች ውስጥ እስካሁን ስልክም ሆነ ኢንተርኔት አለመመለሳቸውን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ በአንድ ወቅት ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።\n\nአገልግሎቶቹን መልሶ በቶሎ ለማስጀመር ያልተቻለው በመሠረተ ልማቶቹ ላይ \"የደረሰው ውድመት በጣም ከፍተኛ\" የሚባል በመሆኑ እንደሆነ በወቅቱ አስረድተዋል።\n\nበመቀሌ የብሮድባንድና የድምፅ አገልግሎት መጀመሩን፣ ከጥር 10 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ውቅሮ፣ እደጋ ሐሙስ፣ አዲግራትና ነጃሺ አካባቢ የድምፅ አገልግሎት በተወሰነ ደረጃ ማግኘት መጀመራቸው ድርጅቱ ገልጾ እንደነበር ይታወሳል።\n\nነገር ግን በስልክ መስመሮች ላይ የደረሰውን ውድመት ምትክ መሣሪያዎችን አግኝቶና በየከተሞቹ በነፃነት ተንቀሳቅሶ ጥገናዎችን ማድረግ እንደተለመደው ቀላል አለመሆኑን በወቅቱ ለቢቢሲ ገልፀው ነበር።\n\nበትግራይ ክልል የተፈጠረው የአገልግሎት መቋረጥ በድርጅቱ ችግር አለመሆኑን ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት የገለፁት ኃላፊዋ፣ በክልሉ ውድመቱ በማን፣ መቼና እንዴት እንደ ደረሰ በጉዳዩ ላይ ምርመራ ያደረገው የፌዴራል ወንጀል ምርመራ ቡድን በቅርቡ ውጤቱን ለሕዝብ ይፋ ያደርጓል ብለው ነበር።\n\nዋና ሥራ አስፈጻሚዋ በትግራይ ክልል የደረሰው የቴሌኮም ውድመት ጥገና በአጭር ጊዜ እንደማይጠናቀቅ በድጋሚ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። \n\n ", "passage_id": "3d0e799fc1b9133e86588a9c1d53b60a" } ]
621350514e487af63cfeb3c71e87d20d
5dd76b59f07d435206f1c1f722dbc95f
«ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለግለሰብ እና ለቡድን ጥቅም ሲባል በእሳት መጫወት አደጋው ከፍተኛ ነው» ሳህለወርቅ ዘውዴ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት
 ዳንኤል ዘነበአዲስ አበባ፦ ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለግለሰብ እና ለቡድን ጥቅም ሲባል በእሳት መጫወት አደጋው ከፍተኛ መሆኑ፤ በእሳት መጫወቱ ካልተጠነቀቁ ማንንም ወደማይምር ሰደድ እሳት እንደሚለውጥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አሳሰቡ።አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በቀን፣ በማታ ያሰለጠናቸውን 4ሺህ 87 የቅድመ ምረቃ ተማሪዎቹን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሰላም ሚኒስትርና ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በተገኙበት ትናንት አስመርቋል። ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት እንደተናገሩት፤ ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለግለሰብ እና ለቡድን ጥቅም ሲባል በእሳት መጫወት አደጋው ከፍተኛ ነው። በእሳት መጫወቱ ካልተጠነቀቁ ማንንም ወደማይምር ሰደድ እሳት ይለወጣል። እኔ ላይ አይደርስም ማለት የዋህነት ነው፤ ይህንን ደግሞ ከሌሎች ሀገሮች መማር ይገባል። በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ንፁሃን ዜጎቻችን እና ለፍቶ አደር ሕዝባችን በማንነት፣ በዘር እና በሃይማኖት ምክንያት ውድ ሕይወታቸውን እጅግ ዘግናኝ በሆነ መንገድ እያጡ መሆኑን የገለጹት ፕሬዚዳንቷ፤ በሕይወት የመኖር መብትን የቀደመ ሌላ መብት ባለመኖሩ በማንኛውም የሀገሪቱ ክፍል ንፁሃን ሕይወታቸውን እንዲያጡ ማንም መፍቀድ እንደሌለበት ተናግረዋል።ከተደገሰልን እልቂት ለማዳን ሕግን የማስከበር ተግባራት በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ ለሁላችንም ተስፋ ሰጪ ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፤ ሞትን እና ቀውስን የሚደግሱልን እንዳሉ አይተናል እያየንም ነው፤ በታሪካችን የሀገራችንን ኅልውናን የሚፈታተኑ አደጋዎች ጥለውብን ካለፉት ጥቁር ጠባሳዎች ተገቢውን ትምህርት ወስደን ማንኛውንም ስጋት አራግፈን በጋራ መነሳት አለብን ሲሉ አሳስበዋል።ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፣ «ዛሬ የተመረቃችሁ ተማሪዎች የሕይወታችሁን አዲስ ምዕራፍ ጀምራችኋል፤ ኢትዮጵያን ነገ የምትመሯት፣ የምታስተዳድሯት፣ የምትታገሉላት፣ በዓለም አቀፍ መድረኮች የምትወክሏት እናንተ ናችሁ። የምትኮሩባት ሀገር ብዙ ተስፋ ያላት መሆኗ የማያጠራጥር ሲሆን፣ ያሳለፍናቸው እና እያሳለፍነው ያለው ጊዜ ግን ብዙ ፈተናዎች የተጋረጠበት ነው። እነዚህ የተጋፈጥናቸው ፈተናዎች ያነጣጠሩት በአንድነታችን፣ በሀገር ሉዓላዊነት፣ በኅልውናችን እና በሰላማዊ ዜጎች በሕይወት የመኖር መሠረታዊ መብት ላይ በመሆኑ ልዩ ትኩረት የሚሹ ናቸው፤ ዛሬ የሕይወታችሁን አዲስ ምዕራፍ ስትጀምሩ ልትጽፉበት የተዘጋጃችሁት አዲስ ነጭ ገጽ በታሪክ ስህተት እንዳይበላሽ፣ እንዳይበከል በእጅጉ ተጠንቀቁ» ሲሉ ተመራቂ ተማሪዎች ኢትዮጵያን እንዲጠብቁ የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል፤ አስገንዝበዋልም። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና በበኩላቸው፤ የዘንድሮው የምረቃ ሥነ ሥርዓት በተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ክስተቶች፣ አስቸጋሪ ሁኔታዎች የተነሳ ከቀደሙት የምረቃ በዓላት በእጅጉ የሚለይ መሆኑን ገልጸዋል። የመማር ማስተማር ሂደቱ በተለይ በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ምክንያት ቢቋረጥም፤ ተማሪዎቹ የማካካሻ ትምህርት መውሰዳቸውን አስታውሰዋል። በዕለቱም ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 4ሺህ 87 የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችንለማስመረቅ መብቃቱን አመልክተዋል። ከተመረቁት አጠቃላይ ተማሪዎች ውስጥ አንድ ሺህ 452 ከምሩቃን ሴት ተማሪዎች ሲሆኑ ከጠቅላላው 35 ነጥብ 5 በመቶ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም ከጠቅላላው ተመራቂዎቹ ውስጥ 48ቱ በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቁ ናቸው ብለዋል። በ1953 ዓ.ም የተቋቋመው አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2012/2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትናንቱን ጨምሮ ለ70ኛ ጊዜ ያስመረቀ ሲሆን፤ በዚህ ዓመት ብቻ በሁለት ዙር ከ10 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል። ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ዲግሪ በማታ ፕሮግራም 809 ተማሪዎችን፣ በቀን 3 ሺህ 39 እንዲሁም በርቀት 18 ተማሪዎቹን ለምርቃት አብቅቷል። ከእነዚህ መሀከል 5045 በመጀመሪያ ዲግሪ፣ 313 በ3ኛ ዲግሪ እና 2226 በማታ ፕሮግራም ያሰለጠናቸው መሆናቸው ተጠቁሟል። እንዲሁም በርቀት 180፣ በክረምት 2252፣ በስፔሻሊቲ 265፣ ከፍተኛ ዲፕሎማ በመምህርነት ፕሮግራም 269 ናቸው። ዩኒቨርሲቲው በዓመቱ በአጠቃላይ 10561 ተማሪዎችን አስመርቋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38229
[ { "passage": "በጉልበት ሳይሆን በእውቀት፣ በስሜት ሳይሆን በስክነት መመራት እንደሚገባ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ፡፡ባለፈው አንድ ዓመት በሀገሪቱ ውስጥ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የተሰሩ ስራዎችና ያጋጠሙ ችግሮች ላይ ያተኮረ መድረክ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አዘጋጅነት በሸራተን አዲስ እየተካሄደ ነው፡፡መድረኩ አዲስ ወግ መርሃ ግብር የሚል ስያሜ ያለው ሲሆን፥ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በመድረኩ ንግግር አድርገዋል፡፡በንግግራቸውም ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ጎዳና ላይ ትገኛለች ብለዋል፡፡ይህ ለውጥ በረከቱ እየጨመረ ፈተናዎች እየቀነሱ ለመጓዝ ምሁራንን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባልም ነው ያሉት።ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ወቅቱ በጉልበት ሳይሆን በእውቀት በስሜት ሳይሆን በስክነት ልንመራና ልንመራበት የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ለዚህ ደግሞ እውቀት መር የሆነ ማህበረሰብን መፍጠር እንደሚያስፈልግም ነው ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ባደረጉት ንግግር የገለፁት፡፡ይህ ሲሆን ስሜታዊነት፣ መንጋነት እና ጀምላ ፈራጅነት የጥፋት እንጅ የልማት መንገድ አለመሆኑን ሁሉም በቀላሉ ሊረዳው ይችላልም ብለዋል በንግግራቸው፡፡ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ተሳታፊዎቹ አራት መሰረታዊ ነገሮችን በትኩረት እንዲሚመለከቱም አሳስበዋል፡፡እነዚህም አብርሆት፣ የሀሳብ ልዕልና፣ የውይይት ባህልና ሂስን የማቅረብ ጥበብን ማስለመድ የምሁራን ሀላፊነት መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡የአብሮሆትን አስፈላጊነት በተናገሩበት ወቅት ፕሬዚዳንቷ እንደገለፁት ምሁራን መንገድን ወለል አድርገው ማሳየት እና የእውቀት አብርሆት እንዲኖር እውቀትን ወደ ህብረተሰቡ መርጨት እንደሚጠበቅባቸው ጠቅሰዋል፡፡በተመሳሳይ የሀሳብ ልዕልና አስፈላጊነትን ያብራሩት ፕሬዚዳንቷ የጉልበት የበላይነት በዚህ ዘመን ሊያበቃ እንደሚገባ አፅዕኖት ሰጥተዋል።ውይይቱ እስከ ነገ ድረስ የሚቀጥል ሲሆን፥ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል።(ምንጭ፡-የጠቅላይ ሚንስትር ፅህፈት ቤት)", "passage_id": "2f94298ee8f3c9638e4d30209f13377a" }, { "passage": "ሶሎሞን በየነአዲስ አበባ:- ለአገር መከላከያ ሠራዊቱ የሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ ሞራል ለመስጠትና አጋርነትን ለማሳየት ያህል ካልሆነ በስተቀር ሠራዊቱ አጥንቱን ከስክሶ አገር እንዳዳነው፣ ደሙን አፍሶ የኢትዮጵያን ሃጢያት እንዳጠበው እንደማይሆን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ ገለጹ።አቶ የሺዋስ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ እንደገለጹት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሰሜን ዕዝ ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ የአገር መከላከያ ሠራዊት ህግን ለማስከበርና የአገርን ህልውና ለማዳን መስዋዕትነት ከፍሏል፤ እየከፈለም ይገኛል። ይሄን ተከትሎም ኅብረተሰቡ ለመከላከያ ሠራዊቱ ሰፊ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ሆኖም በዚህ መልኩ የሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ ለሠራዊቱ ሞራል ለመስጠትና አጋርነትን ለማሳየት ያህል ካልሆነ በስተቀር ማንም ምንም አይነት ድጋፍ ቢያደርግ መከላከያ ሠራዊቱ አጥንቱን ከስክሶ አገር እንዳዳነው፣ ደሙን አፍሶ የኢትዮጵያን ሃጢያት እንዳጠበው አይሆንም።በአገር መከላከያ ላይ የተፈጸመው ክህደት እኛ ካልመራን አገር ትጠፋለች ከሚል አስተሳሰብ የመነጨ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ የሺዋስ፤ ይህ አጥፊ ቡድን እራሱ የቆሰቆሰውን የኤርትራ ጦርነት ምክንያት አድርጎ የአገሪቱ ትልቁ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዲፖ፣ ብረት ለበስ ወታደራዊ ኃይል፣ የአገሪቷ መካናይዝድ ጦር፣ ስምንት ትልልቅ ክፍለጦር ያሁሉ የጦር መሳሪያ በአንድ ቦታ በማከማቸት የየራሱን ጉልበት ሲያጠናክር መቆይቱን ተናግረዋል። የጁንታው ቡድን በህዝብ ቁጣ አንድ ቀን ስልጣኔን አጣለሁ ብሎ ስለሚሰጋ ሰልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ ለጦርነት ሲዘጋጅ እንደቆየና ጉድጓድ ሲቆፍር፣ ነዳጅና የጦር መሳሪያ ሲያከማች ጊዜውን እንዳጠፋ በመግለጽም፤ ከዚህ ባሻገር በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ከለውጥ መንግሥቱ ጋር ተባብሮ ከመስራት ይልቅ በሰበብ አስባቡ ጠብ እየፈለገ ሁከት ለመፍጠር ሲሞክር መቆየቱን አብራርተዋል። በመጨረሻም ቡድኑ ለ21 ዓመታት ያህል ድንበር ሲጠብቅ የቆየውን ሠራዊት ከትግራይ አይወጣም በማለት በሠራዊቱና በመንግሥት ላይ ጫና ለማሳረፍ ከመሞከሩም ባሻገር፤ ለትግራይ ህዝብ አለኝታና መከታ በነበረው ሠራዊት ላይ ጥቃት በመፈጸም ጁንታው ወራዳነቱን አሳይቷል። ይህ ድርጊቱም የትግራይን\nህዝብ ባህልና ማንነት\nየማይገለጽና በታሪክ ታይቶ\nየማይታወቅ አውሬያዊ ስብስብ\nባህሪ ነው ያሉት\nአቶ የሺዋስ፤ ድርጊቱ\nበክርስትናም ሆነ በእስልምናም\nነውርና የተወገዘ መሆኑንም\nአስረድተዋል። ከህዝብ ጋር\nሆኖ አንበጣ ሲከላከል፣\nየህዳሴ ግድብን ሲጠብቅ፤\nሰብል ሲሰበስብ፤ ከሌለው ላይ አዋጥቶ ትምህርት ቤት ሲያሰራ በነበረን የህዝብ ሠራዊት ከኋላው መውጋት ከከሃዲነትም በላይ መሆኑን ገልጸዋል። ቡድኑ የፈጸመው አስጸያፊ ድርጊት ኢትዮጵያንም ሆነ ፖለቲካውን ከአለማወቅ፣ ሃሳባቸውም ያረጀና ያፈጀ መሆኑን ካለመገንዘብ ነው ያሉት አቶ የሺዋስ፤ በመከላከያ ላይ የተሰራው ግፍ ሁሉም ኅብረተሰብ ከራስ ጸጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ ስሜቱ ዘልቆ የተሰማው መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህም በኮቪድ እና ህዳሴ ግድቡ ወቅት ካሳየው የአንድነት ስሜት በላቀ መልኩ የህወሓት ጁንታ ቡድን ህግ መጣሱን ተከትሎ መከላከያ በወሰደው ህግን የማስከበር እርምጃ እንደአንድ ሰው ስሜቱ መተሳሰሩን ተናግረዋል። የህብረተሰቡ አንድነት ደግሞ ለኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋ እንደመሆኑ በዚህ ረገድ ፓርቲዎችን፣ ሽማግሌዎችን፣ የኃይማኖት አባቶችን በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ህዝብ ሊመሰገን ይገባዋል፤ ብለዋል። እንደ አቶ የሺዋስ ገለጻ፤ ህግን ለማስከበርና ሀገርን ለማዳን መከላከያ የወሰደው እርምጃ ሌላም ተመሳሳይ ዕኩይ ባህሪ ላላቸው አካላት አስተማሪ ነው። ሀገር ከማዳኑም ባሻገር ኢትዮጵያ የምትኮራበት ተቋም መገንባት መቻሉንም ያመላከተ ነው። መከላከያ ሠራዊቱ በአጠቃላይ መከላከያ ተቋሙ ምን ያክል ጠንካራ እንደሆነ ያስገነዘበ፤ ከአየር ኃይሉ እስከ እግረኛው ድረስ ከአገር ውስጥ ላለው ቦርቧሪ ከውጭ ለሚያስበውም ወራሪ በጣም ጥሩ ትምህርት የሰጠ እና ጀግኖችን ያፈራ ሂደትም ሆኗል። አምባገነን ሁል ጊዜ ጠብ የሚጭረው ከወጣቱ ባሻገር እናቶችን፣ አረጋዊያንና በሽተኞችን ጭምር ለማስፈጀት ነው ያሉት አቶ የሺዋስ፤ እንደፓርቲ ደም በመለገስ ገንዘብ በመስጠት በምንችለው ሁሉ ከመከላከያ ጎን ቁመናል። ኅብረተሰቡም የሚችለውን ሁሉ ለመከላከያ ድጋፍ እያደረገ ነው። ይህ ድጋፍ እስከመጨረሻ ድረስ እንዲዘልቅ በማድረግ ሁሉም አጋርነቱን ሊያሳይ ይገባል ሲሉ አመልክተዋል። ‹‹ከመከላከያ ጎን ቆማችኋል ተብለው በገመድ ታንቀው የተገደሉ የትግራይ ልጆች አሉ። ይህ ሲታሰብ ያለአግባብ የተከፈለው መስዋትነት በጣም ብዙና ያሚያም ነው” ያሉት አቶ የሺዋስ፤ ፖለቲካ ማወቅ ዓለማወቅ፣ ህዝብ ይቅርታ መቀበል አለመቀበል ሌላ ነገር ሆኖ በተለይ በሰሜን ዕዝ ላይ የፈጸሙት አረመኔያዊ ተግባር ፈጽሞ ከሰውነት የወጡ ከትግራይ ህዝብ ጋር የማይተዋወቁ ከሌላ ዓለም የመጡ ፍጡራን ናቸው እንድንል አድርጎናል ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እኩይ ቡድን ለፍርድ እስኪቀርብ ድረስም ሁሉም ኢትጵያ ህዝብ ከመከላከያና ከጸጥታ አካላት ጎን እንዲቆምም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013", "passage_id": "14de21769223b2b3081f492260b42bb7" }, { "passage": "– ሁሉን ነገር በግጭት ለመፍታት የሚያስቡትን ወጣቱ በቃችሁ ሊላቸው ይገባል – ግድቡ የኢትዮጵያን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ የሚሠራ ነው – ምርጫውን ለማድረግ\nበቂ ዝግጅት አለአዲስ አበባ፡- ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ለህዝብ ተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ባለፈው መስከረም 26 ቀን 2012 ዓ.ም ባቀረቡት የመክፈቻ ንግግር ላይ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ማብራሪያ ሰጡ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ትናንት ሲካሄድ የምክር ቤቱ አባላት በፕሬዚዳንቷ ንግግር ላይ እንዲያብራሩላቸው የፈለጉትን ጥያቄዎች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅርበዋል። ከአባላቱ ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል በተለያዩ አካባ ቢዎች የሚፈጠሩ ግጭቶችን ለማቆም መንግሥት በበጀት ዓመቱ ስለሚወስዳቸው ማስተካከያዎች ማብራሪያ እየተጠየቀበት ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፤ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት 45 ዓመታት በጦርነት በርካታ ወገኖቻችንን ማጣታችንና፤ ለአካል ጉዳትም የተዳረጉ እንዳሉ በማንሳት ሁሉም ቦታ ላይ ግጭት የሚፈጥሩት አንድ አይነት ሰዎች ናቸው ብለዋል። ይህም ከባለፈው አለመማር ነው፤  ሁሉ ነገር በግጭት ነው የሚፈታው ብለው የሚያምኑ አሉ። እነሱ ያስገድላሉ እንጂ አይሞቱም ወጣቱ ይህን ተገንዝቦ እነዚህን ሰዎች በቃችሁ ሊላቸው ይገባል ብለዋል። የግጭትን መሠረታዊ አመጣጥና አፈታት መገንዘብ ጠቃሚ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግጭትን የምንገነዘብበትና የምንፈታበት መንገድ ችግር ያለበት ነው። ግጭትን ሙሉ ለሙሉ ማስቀረት አይቻልም። በተቀናጀ ወይም ባልተቀናጀ መንገድ ችግር ሊፈጠር ይችላል፤ ዋናው ጉዳይ የሕግ አስከባሪውን አቅም መፍጠርና ግጭት ከተፈጠረም ማረም መቻል እንደሆነ አብራርተዋል። በአማራና በትግራይ ክልል መካከል የሚየታየውን መካረር አስመልክቶም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲናገሩም ክልሎቹ ሲሰዳደቡ ቢውሉ ሁለቱ ህዝቦች ለዘላለም አይለያዩም። ሁለቱ ክልሎች በስሜት ተነሳስተው ከተጋጩም በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል ተፈጥሮ ሁላችንም በታሪኩ እንዳፈርነው ይሆናል ብለዋል። “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ የትግራይን ክልል የሚመሩ ጥቂት ግለሰቦች የትግራይን ህዝብ የልማት ችግር ለመፍታት የሚፈልጉ ናቸው። በመሐል ያሉ ናቸው ችግር የሚፈጥሩት እነዚህን መለየት ያስፈልጋል” ሲሉም አክለዋል። አሁን ባለው የፖለቲካ ትኩሳት ድህነትን ሳናሸንፍና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሳይኖረን ክላሽ አይጠቅመንም ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መክረዋል። ቅማንትንና አማራን በሚመለከትም የሚበጀው ቆም ብሎ መወያየት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከአማራ ክልል መንግሥትና ህዝብ በላይ ለቅማንት ህዝብ የሚቀርብ አንድም አካል የለም። ይኸን ጉዳይ በተመለከተ በአብዛኛው ከስምምነት መደረሱንና በሦስት ቀበሌዎችም ያለውን ችግርም በሠላማዊ መንገድ መፍታት እንደሚቻልም ጠቁመዋል። ሁለቱም አካላት ውስጣቸውን አይተው መፍታት ይገባቸዋል። በመካከል እሳት እያቀጣጠሉ የሚሞቁ ግን መኖር አይችሉም ከዚህ ይልቅ ለዘላቂ ሠላም መሥራት ይገባል ብለዋል። ዶክተር አብይ፤ በአሁን ዘመን መንገድ በመዝጋት አይደለም ድንበር በመዝጋት እንኳን ጥቅምን ማረጋገጥ አይቻልም። መንገድ መዝጋት የኋላ ቀርና የብሽሽቅ  ፖለቲካ ውጤት ነው። መንግሥትን ለመቃወምም ሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመሳደብ አዳራሽ የተሰበሰበን ሰው አዳራሽ ገብቶ መረበሽም አግባብ አይደለም። ሰው በሠላማዊ መንገድ እንዲቃወም ካለማመድነው የኋላ ኋላ ወደ አመጽና ግጭት መግባቱ አይቀርም። የአማራንና የኦሮሞን፣ የአማራንና የትግራይን ህዝብ ለይቶ ማስቆም በማይቻልበት ሁኔታ መንገድ መዝጋት ተገቢነት የሌለው የኋላቀር ፖለቲካ አካሄድ ውጤት በመሆኑ ከዚህ መውጣት አለብን ሲሉም ተናግረዋል። አሁን ያለው እሳት የመለኮስ ጉዳይ እየበረደ ይሄዳል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት እርምጃ መውሰድ አቅቶት ሳይሆን እርምጃ መውሰዱ ችግሩን ስለማይፈታው በሆደ ሰፊነት ይዞት ነው ብለዋል። ዜጎችም ይህን ተገንዝበው ለሠላም መትጋት አለባቸው። ችግሩ በኢትዮጵያና በህዝቦቿ ላይ የከፋ ችግር የሚያመጣ ከሆነ ግን መንግሥት እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ ነው። አብዛኛው ለሚያባሉን ሰዎች በባዮሎጂም መልስ ስላለው በቀጣይ ይበርዳል ሲሉም ተስፋ ሰጥተዋል። በምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበላቸው ሌላው ጥያቄ የመገናኛ ብዙሃን አጠቃቀምን፣ በህዳሴ ግድብ ላይ ግብጽ እያነሳቸው ያለው ጥያቄና የምርጫ መካሄድን የተመለከተ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፤ መገናኛ ብዙሃንን በተመለከተ በሰጡት ምላሽ “የውጭ አገር ዜጋ የሆናችሁ የሚዲያ ባለቤቶች፣ የኢትዮጵያ ፓስፖርት የሌላችሁ የሚዲያ ባለቤቶች፤ ስትፈልጉና ሠላም ሲሆን እዚህ ተጫውታችሁ እኛ ችግር ውስጥ ስንገባ ጥላችሁ የምትሄዱበት ሁለት አገር ያላችሁ ሰዎች ትግስት እያደረግን ያለነው አውዱን ለማስፋት ነው። ይሁንና በማንኛውም ሰዓት በኢትዮጵያ ሠላምና ህልውና ላይ ከመጣችሁ አማረኛም ሆነ ኦሮምኛ ብትናገሩም እርምጃ መውሰዳችን የማይቀር መሆኑን በጥንቃቄ መገንዘብ አስፈላጊ ይሆናል። ሁለት ቤት መጫወት አይቻልም፤ እኛ የምንሄድበት አገር የለንም። አገራችን ይሄ ስለሆነ ሠላም እንፈልጋለን። ተቀያሪ ያላችሁ ሰዎች በነፃነት ሠላማችን፣ ልማታችንንና ዴሞክራሲያችንን ካገዛችሁ እሰዬው በደስታ፤ ከዚያ ውጭ ግን ለመነገጃ የምትጠቀሙበት ከሆነ በዚህ ሁኔታ በነፃነትና  በዴሞክራሲ ስም የሚቀለድ እንዳልሆነ ታሳቢ ማድረግ ያስፈልጋል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።የህዳሴ ግድብን በተመለከተም ግድቡ የኢትዮጵያን ጥቅምና ክብር በሚያስጠብቅ መልኩ የሚሠራ ፕሮጀክት ነው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ የግብጽን ህዝብ የመጉዳት ፍላጎት የለውም፤ ከሀብቱ በፍትሃዊነት መጠቀም ነው የሚፈልገው ብለዋል። የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የጀመሩ መሪዎች ሥራን ምርጥ ሥራ ስለሆነ፤ መጨረስ አለብን። በእኛና በግብጽ መካከል የተለየ የሚያነጋግረን አጀንዳ የለም። የግብጽ መንግሥትና ህዝብ ማተኮር ያለበት ኢትዮጵያ የጀመረችውን የአረንጓዴ ልማት በቀጥታ ማገዝ ነው። በህዳሴ ግድብ ላይ እየተነሳ ላለው ማንኛውም አይነት ጥያቄ ችግር ፈጣሪዎቹ እኛ ነን፤ ባስቀመጥነው ልክ ብንጨርሰው ኖሮ አጀንዳ አይሆንም ነበር በማለትም ስለመዘግየቱ ቁጭታቸውን ተናግረዋል። ዶክተር አብይ፤ ምርጫውን አሁን አንችልም በሚቀጥለው እናድርግ ካልን ብዙ ችግር አለው። አሁን ላይ ምርጫውን ማድረግ በብዙ መንገድ ጥቅም አለው። ምርጫውን ለማድረግም በቂ ዝግጅት አለ። ለምርጫ ቦርድ የተመደበው ሀብት ባለፉት አምስት ምርጫዎች ከተመደበው የበለጠ ነው። የምርጫ ቦርድ አደረጃጀት በንፅፅር ከምንጊዜውም በተሻለ ነፃ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ አሸንፎ መምራት ብቻ ሳይሆን ተሸንፎ በሠላማዊ መንገድ ሥልጣን ማስረከብም ትልቅ ታሪክ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫን ተከትሎ የሚፈጠሩ ግጭቶች ምን እንደሚያስከትሉ ከምርጫ 97 ተረድቷል፤ ስለዚህ ምርጫን ተከትሎ የሚነሳን ግጭት አይፈልግም፤ ቢፈጠርም እንዴት እንደሚያልፈው ያውቃል ብለዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች አሸንፈው\nመንግሥት በመሆን ብቻ\nየሚያምኑ ከሆነ የፖለቲካን\nሙሉ ቅርፅ አያሳይም፤\nመሸነፍንም መለማመድ ያስፈልጋል።\nበቤተሰብ፣ በጓደኛ በማህበር\nየፖለቲካ ፓርቲ መመስረት\nአያዋጣም፤ ለኢህአዴግ ጭምር\nሰብሰብ ማለት ነው\nየሚበጀው ሲሉ ከመለሱ\nበኋላ መንግሥትንና ፓርቲን\nእንዲሁም ፓርቲንና ኢትዮጵያን\nአንድ አድርጎ ማየት\nተገቢ አለመሆኑንም ተናግረዋል።\n አዲስ  ዘመን ጥቅምት 12/2012አጎናፍር ገዛኸኝ ", "passage_id": "f1b57e26581606f352e53482daf472c6" }, { "passage": "አበባ ፣ ሚያዚያ 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የበላይ ጠባቂ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የኮቪድ19 ወረርሽኝን በተመለከተ ከማህበሩ አመራሮች ጋር ተወያዩ።በውይይታቸውም ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ማህበሩ ወረርሽኙን በመከላከል ሂደት ውስጥ ያለውን ቁልፍ ሚና የበለጠ እንዲያጠናክር መልዕክት ማስተላለፋቸውን ከፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ኮቪድ19ን ለመከላከል በተለያዩ ከተሞች የኬሚካል ርጭት በማከናወን፣ በጎ ፈቃደኞችን በማሰማራት እና የንፅህና መጠበቂያዎችን በማሰራጨት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል።", "passage_id": "0df949267eed8d82460356daa6639066" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ባህልን ጠብቆ ማቆየት አንድነትን፣ መተባበርንና ለአንድ ዓላማ አብሮ መቆምን ማሳያ በመሆኑ፤ ሁሉም ይሄን ተገንዝቦ በጋራ ልንንከባከባቸው እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ተናገሩ። ትናንት በሚሊኒየም አዳራሽ በተካሄደ የአሸንድዬ፣ ሻደይና ሶለል በዓል ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፣ ድንበር የለሹን ባህልና ቅርስ ጠብቆ ማቆየት አንድነትንና መተባበርን እንዲሁም ለአንድ ዓላማ መቆምን ማሳያ ነው። በመሆኑም ባህሎችን ጠብቆ ማቆየትና ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለም ሀብት እንዲሆኑ ለማድረግ ሁሉም የሚጠበቅበትን መወጣት ይኖርበታል። እንደ ፕሬዚዳንቷ ገለጻ፣ አሸንድዬ፣ ሻደይና ሶለን በዓል ምንም እንኳን የሴቶች በዓል ቢሆንም በርካታ ወንዶችም መሳተፋቸው ኢትዮጵያ ላላት የባህል እሴት ያላቸውን ክብር የሚያሳይ ነው። ኢትዮጵያ ደግሞ በርካታ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች ያሏት፤ ከአፍሪካ ቀዳሚ በመሆንም በርካታ ቅርሶችን በዩኔስኮ አስመዝግባ የዓለም ቅርስ ያደረገች አገር ናት። እነዚህ ቅርሶች ደግሞ የኢትዮጵያውያን ብቻ ወይም የአንድ ቦታ ብቻ አይደሉም። የአሸንድዬ፣ ሻደይና ሶለን በዓልም የአንድ፣ የሁለት ወይም የሶስት ክልል ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ብሎም የዓለም ቅርስ እንዲሆን እንደ መስቀል በዓል፣ እንደ ፊቼ ጨምባላላ፣ እንደ ገዳ ስርዓት ሁሉ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣና በመተባበርም በዩኔስኮ ለማስመዝገብ መስራት ይጠበቅበታል። ‹‹ቅርሶች አሉን ስንል ለዘመናት እነዚህ ቅርሶች እንዲቆዩ የታገሉ እናቶችና አባቶቻችን ያወረሱን ናቸው። ለብዙ መቶ ዓመታት ባላቸው እውቀት፣  ሰርተውና ገንብተው እንደገናም ንብረት እንዲሆኑ፤ ለትውልድም እንዲተላለፉ አድርገው ያቆዩልን ናቸው›› ያሉት ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ፤ እነዚህን ቅርሶች ድንበር የለሽ መሆናቸውን እና ባህልን ጠብቆ ማቆትም የአንድነት፣ አብሮነትና ለአንድ ዓላማ በጋራ መቆየትን ማሳያ መሆኑን ተገንዝቦ ባህሎችን ተንከባክቦ ማቆየት የዚህ ትውልድ ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል። የሻደይ፣ አሸንድዬና ሶለን በዓል ሴቶችን የሚመለከትና ለሴቶችም ነጻነትን የሚሰጥ እንደመሆኑ በየዓመቱም ለሁለትና ሶስት ብሎም ለሳምንት ከማክበር በዘለለ የሴቶች ነጻነት ዓመቱን ሙሉ ማክበር እንደሚገባ አሳስበዋል። ለሴቶች መሰረታዊ መብቶች መከበር መስራት እንደሚገባ በመግለጽም፤ ቀጣዩ ዓመትም የሴቶችን እምርታ ወደፊት ማስኬጃ መሆን እንደሚገባው ተናግረዋል። በበዓሉ\nላይ\nየክልሉ\nፕሬዚዳንት\nአቶ\nተመስገን\nጥሩነህ፣\nየአዲስ\nአበባ\nከተማ\nከንቲባ\nኢንጂነር\nታከለ\nኡማ፣\nየባህልና\nቱሪዝም\nሚኒስትሯ\nዶክተር\nሂሩት\nካሳውን\nጨምሮ\nየክልሉና\nየፌዴራል\nመንግሥት\nኃላፊዎች\nተገኝተዋል።\n አዲስ ዘመን ነሃሴ 20/2011ግርማ መንግሥቴ ", "passage_id": "6abf0ce4b939798bbe7c57b820863885" } ]
b4f1963fe331f8e04cebbd923b798719
cc43bb70bb93e1c5e8505ddb81f7982a
ፌዴሬሽኑ አሰልጣኞችን መረጠ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቶኪዮ ኦሊምፒክ ተሳታፊ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኞችን ስም ዝርዝር አስታወቀ። ፌዴሬሽኑ በቅርቡ ወደ ዝግጅት ምዕራፍ እንደሚገባም ይጠበቃል። በጃፓን አስተናጋጅነት የሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ የወራት እድሜ ብቻ የቀረው መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወደ ዝግጅት ለመግባት የሚያስችለውን የአሰልጣኞች ምርጫ ማድረጉን አስታውቋል። ፌዴሬሽኑ ምርጫውን ባዘጋጀው መስፈርት መሰረት አወዳድሮ ያከናወነ መሆኑንም በድረ ገጹ አስነብቧል። ፌዴሬሽኑ በአፋጣኝ ወደ ስልጠና ለመግባት በሚያስችሉ ሁኔታዎች ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅርቡ ምክክር ማድረጉ የሚታወስ ነው። ከስድስት ወራት ያነሰ ጊዜ ብቻ ለቀረው ውድድር ካለፉት የሪዮ ኦሊምፒክና የዶሃ ዓለም ሻምፒዮና ተሞክሮ በመውሰድ ስልጠና እንዲታቀድና በአፋጣኝ ወደ ትግበራ እንዲገባ ሁኔታዎች እንዲመቻቹም አቅጣጫ አስቀምጧል። ለተግባራዊነቱም ፌዴሬሽኑ በሚያወጣው የምልመላና የስልጠና ዝግጅት ሚናውን እንደሚወጣ ባስታወቀው መሰረት የአሰልጣኞችን ምርጫ ያከናወነ ሲሆን፤ በቅርቡ አትሌቶችን በመምረጥ ወደ ስልጠና እንደሚገባም ይጠበቃል። ምርጫው እርምጃን ጨምሮ ኢትዮጵያ በምትታወ ቅባቸው አምስት ርቀቶች ተደርጓል። በዚህም መሰረት በመካከለኛ ርቀት አሰልጣኝ ብርሃኑ መኮንን፣ ሃብታሙ ግርማ፣ ኢሳ ሽቦ እና ጉዲሳ ታሱ ተመርጠዋል። አሰልጣኝ አብርሃም ኃይለማሪያም እና ስንታየሁ ካሳሁን ደግሞ በተጠባባቂነት የሚቆዩ ይሆናል። በ3ሺ ሜትር ደግሞ አሰልጣኝ ተሾመ ከበደ እና ዶክተር ብዙአየሁ ታረቀኝ ሲመረጡ አሰልጣን ከፍያለው አለሙ ተጠባባቂ ሆነዋል። ሃገሪቷ በኦሊምፒክ መድረክ በተለይ ውጤታማ በሆነችባቸው የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር ርቀቶችም አራት አሰልጣኞች ተመራጭ ሆነዋል። አሰልጣኝ ሁሴን ሸቦ፣ ቶሌራ ዲንቃ፣ ንጋቱ ወርቁ እና ኃይሌ እያሱ ሲመረጡ፤ አሰልጣኝ ተፈሪ መኮንን እና በሪሁን ተስፋይ ደግሞ የተጠባባቂነት ስፍራን ይዘዋል። በረጅሙ የአትሌቲክስ ውድድር ማራቶን በማናጀር አሰልጣኝነት ስኬታማ የሆኑት አሰልጣኝ ሃጂ አደሎ ከሌላው አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ጋር በመሆን የርቀቱን እንደሚመሩም በዝርዝሩ ተመልክቷል። አሰልጣኝ ጌታነህ ተሰማ እና ይረፉ ብርሃኑ ደግሞ ተጠባባቂ ሆነው ተመርጠዋል። የእርምጃ ቡድኑም በሻለቃ ባየ አሰፋ አሰልጣኝነት ወደ ቶኪዮ የሚያመራ ይሆናል። ፌዴሬሽኑ ምርጫውን ያሳወቀው ከትናንት በስቲያ ሲሆን፣ በምርጫው ላይ ቅሬታ ያለው አካል እስከ ዛሬ ድረስ ጉርድ ሾላ በሚገኘው ጽህፈት ቤቱ በመገኘት ማሳወቅ እንደሚችልም ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን ረቡዕ የካቲት 11/2012ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27523
[ { "passage": "በካፍ ኢንስትራክተር ሽፈራው እሸቴ አሰልጣኝነት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ስፖርት እና ትምህርት ስልጠና ማዕከል በተሰጠው ስልጠና በከተማው የሚገኙ ከ20 በላይ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ዳኞች ተካፍለዋል። ትላንት በተጀመረው ስልጠና ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት ኃይለየሱስ ፍስሀ (ኢንጅነር) በከተማችን እግር ኳስን በዘመናዊነት ለመምራት ቁልፍ የሆኑ ዳኞች ከአዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎች ጋር ራሳቸውን እያበቁ ሙያውን በብቃት እንዲመሩ ታስቦ መሰጠቱን ተናግረዋል። በተለይ በዘርፉ የካበተ ዕውቀትና ልምድ ያላቸው ኢንስትራክተር ሽፈራው እሸቴ ለ2 ቀናት መስጠታቸው ልዩ ዕድል መሆኑን ነው ፕሬዝዳንቱ የገለፁት። ትኩረቱን በተሻሻሉ አዳዲስ የዳኝነት ህጎች ላይ መሰረት ባደረው በዚህ ስልጠና ሰልጣኞች ጠቃሚ ነገሮች እንዳገኙበት ተናግረው ፌዴሬሽኑ ይህንን ስልጠና በቀጣይ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።በሌላ ዜና የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን የውስጥ ውድድሮች የሆኑት የከፍተኛ ዲቪዝዮን፣ አንደኛ ዲቪዝዮን እና የሴቶች ውድድር የጀመረ ሲሆን የኤምአርአይ ምርመራው በተለያዩ ምክንያቶች በፍጥነት አለመጠናቀቁን ተከትሎ ከ17 ዓመት በታች የወንዶች ውድድር እስካሁን ያልጀመረ መሆኑ ታውቋል። በቅርቡ ውድድሩን ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ መሆኑ እና ውድድሩ የሚካሄድባቸውን ሜዳዎች በበቂ ሁኔታ እድሳት እየተደርጎላቸው ለጨዋታው ዝግጁ እንደተደረጉም ተነግሮናል።", "passage_id": "e10cd5add2b4f73668c5c1579d651eba" }, { "passage": "የከፍተኛ ሊጉ ክለብ አዲስ አበባ ከተማ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ወደ አንደኛ ዲቪዝዮን ላደገው የሴቶች ቡድኑ አሰልጣኝ ሲቀጥር የቴክኒክ ዳይሬክተርም ሾማል። ክለቡ በቀጣይ ቀናት ለወንዶች ቡድኑ አዲስ አሰልጣኝ እንደሚሾምም ይጠበቃል።መሰረት ማኒ አዲሷ የአዲስ አበበ ከተማ ሴቶች ቡድን አሰልጣኝ ሆና ለቀጣዮቹ ሁለት የውድድር ዓመታት የምትመራ ይሆናል። የቀድሞዋ የድሬዳዋ ከተማ ወንዶች ቡድን እና የሉሲዎቹ አሰልጣኝ መሰረት ከብሔራዊ ቡድን ከተለያየች በኋላ በታዳጊዎች ስልጠና ላይ ስትሰራ የቆየች ሲሆን አዲሱን የውድድር ዘመን ወደ አንደኛ ዲቪዝዮን ባደገው የዋና ከተማው ክለብ የምንመለከታት ይሆናል። መሠረት በ2007 ድሬዳዋ ከተማን ለፕሪምየር ሊግ በማብቃት በታሪክ የመጀመርያዋ ሴት የፕሪምየር ሊግ ክለብ አሰልጣኝ በመሆን ታሪክ መስራቷ የሚታወስ ነው። ከለቡ በቴክኒክ ዳይሬክተርነት የቀጠረው ዳንኤል ገብረማርያምን ነው። አቶ ዳንኤል በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ቴክነክ ዲፓርትመንት ውስጥ የሰሩ ሲሆን ለአጭር ጊዜም የቴክኒክ ዳይሬክተር ሆነው አገልግለዋል። የተጠኔቀቀው የውድድር ዓመትን ደግሞ በአዳማ ከተማ አሳልፈዋል። አቶ ዳንኤል እንደ መሠረት ሁሉ የሁለት ዓመት ውል እንደተሰጣቸው ከክለቡ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በከፍተኛ ሊግ የሚወዳደረው የአአ ከተማ ወንዶች ቡድን በ25ኛው ሳምንት ከአሰልጣኙ አስራት አባተ ጋር ከተለያየ በኋላ ዋና አሰልጣኝ ሳይቀጥር የቆየ ሲሆን መኮንን ገብረዮሀንስን አሰልጣኝ አድርጎ ለመሾም መቃረቡ ታውቋል። አሰልጣኝ መኮንን ከዚህ ቀደም ከዳሽን ቢራ፣ ኢትዮጵያ ውሀ ስፖርት እና ጅማ አባ ጅፋርን ወደ ፕሪምየር ሊግ ማሳደግ ችለዋል።", "passage_id": "6532ff0edbe743bb0155c5145bfa06bd" }, { "passage": "የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ከፊፋ ጋር በመነጋገር ዛሬ ረፋድ ላይ በርከት ያሉ አሰልጣኞች የተካፈሉበት ውይይት በዙም (Zoom) አማካኝነት አድርገዋል።ለአርባ ደቂቃ በፈጀው በዚህ ስልጠና ላይ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንት አቶ ኢሳይያስ ጅራ ፣ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የወቅቱ አሰልጣኝ አብርሐም መብራቱ፣ የቴክኒክ ኮሚቴው ኃላፊ መኮንን ኩሩ፣ አሰልጣኝ አብርሐም ተክለሐይማኖት፣ አንጋፋው አሰልጣኝ ጋሽ ከማል እና በታዳጊ ቡድኖች ላይ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ ብዛት ያላቸው አሰልጣኞች በኮንፈረሱ ላይ ተካፋይ ሆነውበታል።ዘጠኝ ሰዓት በጀመረው በዚህ ስልጠና ፊፋን በመወከል Jose Ramon Capdevila (ከስፔን) በዋናነት የስልጠናቸው ትኩረት ያደረገው ኢትዮጵያ የታዳጊ ፕሮጀክቶችን የአሰለጣጠን መንገዷ በምን መልኩ ቢሆን ሀገር ሊያሳድግ ይችላል። እንዴት ተደርጎ ነው የተሻሉ ተፎካካሪ ተጫዋቾችን በማውጣት ለብሔራዊ ቡድን ማድረስ የሚቻለው እና የሀገሪቱን እግርኳስ ለማሳደግ እንዴት ማሻሽል እንደሚቻል የዛሬው ስልጠና የተመለከታቸው ነጥቦች ናቸው።በቀጣይ ከ15 ቀን በኃላ በተመሳሳይ በዚሁ የታዳጊዎች ስልጠና ዙርያ ኮንፍረሱ እንደሚቀጥል ለማወቅ ችለናል።", "passage_id": "83fdd25ca66bd23fb4f69b27d38773ed" }, { "passage": "በጃፓኗ መዲና ቶኪዮ የሚከናወነው የ2020 ኦሊምፒክ ላይ በሴቶች እግርኳስ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጀመርያ የማጣርያ ጨዋታውን ከዩጋንዳ ጋር በመጋቢት ወር መጨረሻ የሚያከናውን ሲሆን ለዚህም ዝግጅት ይረዳ ዘንድ ከወዲሁ አሰልጣኝ ለመቅጠር ዛሬ የቅጥር ማስታወቂያ ወጥቷል።ፌዴሬሽኑ ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ላይ ከተጠቀሱ መስፈርቶች መካከል በሴቶች ሊግ ላይ ሦስት እና ከዚያ በላይ ዓመታት የማሰልጠን ልምድ እንዲሁም ውጤት ያላት፣ ከካፍ የስራ ቋንቋዎች አንዱን የምትናገር፣ 10ኛ ክፍል በላይ የሆነች እና ከቢ ላይሰንስ በላይ ያላት፣ የአስተዳደራዊ እና የስልጠና ዕቅዷን የምታቀርብ እና በዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆነች ይጠቀሳሉ።ተወዳዳሪዎች መመዝገብ የሚችሉት እስከ የካቲት 29 እንደሆነ ሲገለፅ በመጋቢት ወር ላይ አሸናፊዋ አሰልጣኝ ይፋ እንደምትደረግ ይጠበቃል።ኢትዮጵያ ከዩጋንዳ ጋር ከመጋቢት 23 እስከ መጋቢት 30 ባሉት ቀናት በደርሶ መልስ የምታከናውን ሲሆን የመጀመርያው ጨዋታ አዲስ አበባ ላይ ይከናወናል። ዩጋንዳን ካለፈች ደግሞ በቀጣዩ ዓመት መጀመርያ ከካሜሩን ጋር በሁለተኛ ዙር ማጣርያ የምትገናኝ ይሆናል።", "passage_id": "eb1d13b16968ac1366b18541c4676f3d" }, { "passage": "የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የንግድ ባንክ የሴቶች ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት ብርሀኑ ግዛውን የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ በማድረግ ሾሟል፡፡በቀጣዩ ወር ኅዳር መጀመሪያ ላይ በታንዛኒያ አስተናጋጅነት የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ ውድድር የሚደረግ ሲሆን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎችም ይከተላሉ። በቅርቡ ከአሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ጋር የተለያየው ፌዴሬሽኑም ለውድድሮቹ ዝግጅት እንዲረዳው ብርሀኑ ግዛውን በዋና አሰልጣኝነት መሾሙን አሰልጣኙ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በየካ እና ሴንትራል ዩኒቨርሲቲ ክለቦች እንዲሁም ከ2004 ጀምሮ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ክለብን በማሰልጠን ላይ የሚገኙት አሰልጣኙ ከዚህ ቀደም በሊሱዎቹ የአሰልጣኝ ሥዩም ከበደ እና አብርሀም ተክለሀይማኖት ረዳትነት እንዲሁም በ2008 በዋና አሰልጣኝነት ሰርተዋል፡፡አሰልጣኙ ነገ ረዳቶቻቸውን እና የተመረጡ ተጫዋቾችን ይፋ የሚያደርጉ ሲሆን ዝግጅታቸውን ደግሞ በዚህ ሳምንት ሀዋሳ ወይም አዲስ አበባ ላይ ሊጀምሩ እንደሚችሉ ሰምተናል፡፡ኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በታንዛኒያ በሚካሄደው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ላይ በምድብ ለ ከዩጋንዳ፣ ኬንያ እና ጅቡቲ ጋር መደልደሉ ይታወሳል።", "passage_id": "a72a53359e581c769dc92b26f90e7b26" } ]
e56c91fec4578a4c41148dbccd5e9ec5
f1eb6ab8101ac38ce8efa30ae780b568
«የትግራይ ሕዝብና ህወሓት አንድ ሆነው አያውቁም፤ ህወሓት ሳይፈጠር የትግራይ ሕዝብ ነበር»የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች
መቀሌ(ኢዜአ)፡- «የትግራይ ሕዝብና ህወሓት አንድ ሆነው አያውቁም፤ ህወሓት ሳይፈጠር የትግራይ ሕዝብ ነበር ወደ ፊትም ይኖራል» ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ትናንት ተወያይቷል።የመድረኩ ተሳታፊ የነበሩት የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች «የህወሓት ቡድን» በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰውን ጥቃት ያወገዙ ሲሆን፤ ቡድኑ በመከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰው ጥቃት የትግራይን ሕዝብ የማይወክልና ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ድርጊት መሆኑንም ነው የተናገሩት።ከዚህ ቀደም የፓርቲና የመንግሥት ሥራ ተደበላልቆእንደነበረ ያስታወሱት ነዋሪዎቹ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከዚህ ተምሮ ማስተካከል እንዳለበት የገለጹት ነዋሪዎቹ፤ «የትግራይ ሕዝብና ህወሓት አንድ ሆነው አያውቁም፤ ህወሓት ሳይፈጠር የትግራይ ሕዝብ ነበር ወደ ፊትም ይኖራል» ብለዋል። በከተማዋ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር ሕዝባዊ ፖሊሶች በአግባቡ ተደራጅተው ወደ ሥራ እንዲገቡም ጠይቀዋል። የትግራይ ሕዝብ ከስጋት ነፃ እንዲሆን የጁንታው አባላት ታድነው ለሕግ መቅረብ ይኖርባቸዋል ያሉት ነዋሪዎቹ፤ ለዚህም ሕዝቡና የፀጥታ ኃይሉ እንዲሁም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ተባብረው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል። በመቀሌ ከተማ የተቋረጠው የባንክ፣ የትራንስፖርትና የኢንተርኔት አገልግሎት በአስቸኳይ እልባት አግኝቶ ሥራ እንዲጀምርም ጠይቀዋል። «በሰሜን ዕዝ ላይ የህወሓት ቡድን ያደረሰው ጥቃት ሕዝቡን እንደማይወክል እንረዳለን» ያሉት በመከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል በላይ ስዩም፤ መከላከያው ወንጀለኞችን ከማደንና መልሶ ግንባታ በተጓዳኝ በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲኖር ሌት ተቀን እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ በበኩላቸው፤ መንግሥት ጉዳት የደረሰባቸውን መሠረተ ልማቶች በመልሶ የመገንባት ሥራ ላይ ርብርብ እያደረገ መሆኑን ያስረዱ ሲሆን፤ በአጭር ጊዜ ውስጥም በርካታ የመሠረተ ልማቶች ወደ ሥራ እንደሚገቡ አረጋግጠዋል። የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ዶክተር አብርሃም በላይ በበኩላቸው፤ «ከዚህ በኋላ በትግራይ ክልል የሰላም፣ የአንድነትና ልማት ጉዳይ በትኩረት ይሰራል» ብለዋል።  አሁን ላይ መቀሌ ከተማ ሰላምና መረጋጋት በመፈጠሩ በርካታ ማህበራዊ አገልገሎቶች በመከናወን ላይ መሆናቸውም ታውቋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38227
[ { "passage": "በቅርብ ግዜ በትግራይ ክልል \"ትግራይ ሃገር መሆን አለባት\" በማለት በሰላማዊ መንገድ ትግል ለማካሄድ የተመሰረት የትግራይ ነፃነት ፓርቲ (ውድብ ናፅነት ትግራይ) ስለያዘው ፕሮግራም ሪፖርት ማቅረባችን ይታወቃል።ትግራይ ከኢትዮጵያ ተነጥላ የራስዋ ሃገር ትመስርት በሚል ጉዳይ ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲና ሉአላዊነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዓምዶም ገብረስላሴ አስተያየታቸውን ጠይቀናል።\n", "passage_id": "e09330707c60464b54aa72522fb1a250" }, { "passage": "እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ ለዚህ ሁሉ\nመሰሪነትና\nለጥፋት\nስትራቴጂው\nህወሓት\nጁንታው\nአገር\nእንዲያተራምስ\nበማድረግ\nየትግራይ\nክልልም\nአሁን\nለገባበት\nምስቅልቅል\nየአቶ\nስብሃት\nነጋ\nመሰሪነት\nትልቁን\nቦታ\nየሚይዝ\nበመሆኑ\nየእርሳቸው\nበቁጥጥር\nስር\nመዋል\nትልቅ\nፖለቲካዊ\nድል\nመሆኑን\nየትግራይ\nዴሞክራሲያዊ\nፓርቲ\nአስታወቀ።\nየፓርቲው ምክትል\nሊቀመንበር\nአቶ\nመስፍን\nደሳለኝ\nከአዲስ\nዘመን\nጋዜጣ\nጋር\nባደረጉት\nቃለ\nምልልስ\nእንደገለጹት\n፣አቶ\nስብሃት\nነጋ\nበውሸትና\nበወንጀል\nእንዲሁም\nለራሳቸው\nከሚገባው\nበላይ\nዋጋ\nሰጥተው\nሕዝቡ\nውስጥ\nየገቡ\n፣ከዛም\nአልፎ\nአንዳንዶች\nእስከማምለክ\nድረስ\nየደረሱላቸው\nግለሰብ\nናቸው፤\nመላው\nሕዝብ\nእንደሚያውቀውም\nከነቤተሰባቸው\nእንደውም\nእስከ\nዘር\nማንዘራቸው\nስልጣንን\nተቆጣጥረው\nትግራይን\nእንዲሁም\nኢትዮጵያን\nበእጅ\nአዙር\nሲመሩ\nኖረዋል\n።ለእርሳቸውና ለዘሮቻቸው\nስልጣን\nማራዘሚያም\nየትግራይ\nሕዝብ\nትልቅ\nማጥ\nውስጥ\nእንዲገባ\nመገደዱን\nያመለከቱት\nአቶ\nመስፍን\n፣\nየግለሰቡ\nመያዝ\nየፖለቲካዊ\nድል\nነው\nእንደውም\nእግዚአብሔር\nአገሪቱን\nከከፋ\nጥፋት\nለመታደግ\nያሰበም\nይመስለኛል\nብለዋል።እንደ አቶ\nመስፍን\nገለጻ\n፣\nየህወሓት\nየትግል\nታሪክ\nሲነሳ\nመልካም\nጎን\nየነበረው\nቢሆንም\nእንደ\nአቶ\nስብሃት\nነጋ\nያሉ\nጽንፍ\nየያዙ\nሰዎች\nትግሉን\nወዳልሆነ\nአቅጣጫ\nበመምራታቸውና\nበዓለም\nላይ\nመጥፎ\nየፖለቲካ\nታሪክ\nያላቸውን\nየእነ\n“ስታሊን”\nን\nአካሄድ\nበመከተላቸው\nየመጠፋፋት።\nየመጠላለፍ\nፖለቲካ\nውስጥ\nገብተው\nየትግራይ\nህዝብ\nትግል\nፍሬ\nእንዳያፈራ\nእንዲሁም\nአሁን\nለገባበት\nትልቅ\nችግር\nመንስኤ\nመሆናቸውን\nአብራርተዋል።ለዚህ\nሁሉ\nመሰሪነትና\nለጥፋት\nስትራቴጂው\nየህወሓት\nጁንታ\nአሁን\nአገርን\nለማተራመስ\nለገባበት\nመንገድ\nትልቅ\nአስተዋጽኦ\nእንደነበራቸው\nየገለጹት\nአቶ\nመስፍን፣\nአሁን\nበቁጥጥር\nስር\nመዋላቸው\nደግሞ\nበትግራይም\nበመላው\nአገሪቱም\nየህወሓት\nጁንታ\nተመልሳ\nትመጣለች\nበማለት በተስፋ\nየሚጠብቁ ሞኞች ተስፋቸውን\nቆርጠው ወደራሳቸው እንዲመለሱና\nሥራቸውን እንዲቀጥሉ እንደሚያደርግም\nጠቁመዋል።አቶ ስብሃት ነጋ በጣም ተንኮለኛ። በቀለኛ። በሰፈር የሚያስቡ በአምባገነናዊ ዴሞክራሲ የተሸፈኑ ከመሆናቸውም በላይ የህወሓትንም ታሪክ አበላሽተዋል ያሉት አቶ መስፍን፣ ለዚህ ሁሉ ችግርም ዋናው ተጠያቂና ምክንያት እርሳቸው ናቸው።በመካከላቸው አንዳንድ በአስተሳሰባቸው ሻል ያሉ ችግሩ እዚህ ከመድረሱና ወደጦርነት ከመገባቱ በፊት በሰላማዊ መንገድ እንደራደር የሚል ሃሳብን ሲያቀርቡ ተጽዕኖ በማድረጋቸው ምክንያት ይህ ጦርነት ተጀምሮ የሰው ህይወት ጠፋ ፣ ንብረት ወደመ ብለዋል።አቶ ስብሃት የራሳቸው ቡድን። ኃይል ።ሰላይ ያላቸው በሁሉም ቦታዎች በሃይማኖቱም በባህሉም በታሪኩም ላይ ገብተው የፈለጉትን ነገር የማድረግ አቅም የፈጠሩ ናቸው ያሉት አቶ መስፍን፣ ከዚህ የተነሳ ሰውየውን እንደ አንድ ሰው ብቻ ማሰብ በጣም ከባድ ነው።በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ትልቅ ነገር የሚሆነው ከዚህ አንጻር እንደሆነም አብራርተዋል። “የትግራይ ህዝብ ለ 17 ዓመት በዱር በገደሉ ያደረገውን ተጋድሎ ። የገበራቸውን ልጆቹን ደም በከንቱ ያስቀሩ፣ ሁሉንም ድካሙን በዜሮ እንዲባዛ ያደረገው የእኚህ ሰው ሴራና ተንኮል ነው፤ አሁን የችግሩ ምንጭ በመነቀሉ ከዚህ በኋላ ክልሉም ሰላም ሰፍኖበት ወደ ልማትና መልሶ ግንባታው ይገባል “ ብለዋል ።አሁን ከባለፈው ታሪካችን ተምረን ብዙ ነገሮችን ማሻሻል መተው የሚገባን መተው ያለብን ይመስለኛል ያሉት አቶ መስፍን፣ ምክንያቱም የሴራ ፖለቲካ የመጠላለፍና ጥሎ የማለፍ አካሄድ ለእነ አቶ ስብሃት ነጋም እንዳልጠቀመ እየታየ ነው፤ በትግራይም ሆነ በመላው የአገሪቱ ክፍል እኛና እናንተ እየተባለ የሚሄድ ፖለቲካ ከዚህ በኋላ ማብቂያው እንደሚሆን አመልክተዋል ።ጊዜያዊ አስተዳደሩም በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደጀመረው ሁሉን አቀፍ የሆነ፣ ማንንም ያላገለለ እና የጋራ ጥቅምን የሚያስጠብቅ ሊሆን እንደሚገባ አመልክተው ፣ ይህ መሆን ከቻለ ፍትህ ማስፈን። ዴሞክራሲን ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል ። እኛም እንደ ፓርቲ አንድነቷንና እኩልነቷን አስጠብቃ የምትቀጥል አገር እንድትኖር ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል።በቀደመው ጊዜ ከፍተኛ የሆነ ብልሽት ከገጠማቸው ተቋማት መካከል መከላከያ ሰራዊት አንዱ ነበር ያሉት አቶ መስፍን ፣አሁን መከላከያ የታነጸበት አካሄድ በጣም አስገራሚ የአጭር ጊዜ ስራ ውጤት የማይመስል የሕዝብ አለኝታ እንዲሆን ማድረግ ያስቻለ እንደሆነ አስታውቀዋል ።በዚህ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ላይም ያሳየው አገር ወዳድነት ፣ቆራጥነትና ለመስዋዕትነት መዘጋጀት አስገራሚ ከመሆኑም በላይ እነዚህን ለሁለት ዓመት ሲዘጋጁ የነበሩ የጥፋት ቡድኖችን ከተቀበሩበት ጉድጓድ በዚህ መልኩ እያደነ ማምጣቱ የሚደነቅ ነው ብለዋል ።በቀጣይም የትግራይን ክልል በማረጋጋት ሰላሙን በማረጋገጥ መልሶ ማቋቋም ላይ ከፍተኛ ድርሻውን እንደሚወጣ ጥርጥር እንደሌላቸው ገልጸዋል።የቀሩት የጁንታው ቡድን አባላትም ከዚህ በኋላ ወዴትም መሄድ ምንም ማድረግ እንደማይችሉ ተገንዝበው በሰላም እጃቸውን ሰጥተው ለፍርድ ቢቀርቡ ለእነሱም መልካም ነው፤ አልያ ግን የተዳፈሩት የመከላከያ ሰራዊት በፍጹም ጀግንነት ከተደበቁበት ጉድጓድ ፈልፍሎ እንደሚያወጣቸው መገንዘብ እንዳለባቸውም አመልክተዋል።አዲስ ዘመን ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም ", "passage_id": "ef81bfce1f9de777e40845c8eb52b3b8" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- የትግራይ ህዝብም በኢትዮጵያ ለውጥ እንዲመጣ መታገሉን የአረና መስራች እና የመድረክ ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አመራር አቶ ገብሩ አስራት ተናገሩ፡፡ አቶ\nገብሩ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ የኢኮኖሚ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት፤ የዴሞክራሲ፣ የነፃነት እና ሌሎችም ብዙ ጥያቄዎችን አንግቦ ከአንድ ዓመት በፊት በነበሩት ሶስት ዓመታት ላይ ይካሄድ በነበረው የለውጥ ጥያቄ ላይ የትግራይ ህዝብም ታግሏል። ከአራት ዓመት በፊትም ‹‹ህወሓት የትግራይ ህዝብን አይወክልም›› ብሎ በሰልፍ ተቃውሞ አሰምቷል፡፡ ታጣቂዎች ህዝቡን ቢያስፈራሩትም ሰልፍ ወጥቶ እስከመታገል ደርሶ እንደነበር የተናገሩት አቶ ገብሩ፤ እምባሰነይቲ የሚባል አካባቢ 30ሺ ህዝብ\nወጥቶ ህወሓትን እንደማይፈልግ ገልጿል ብለዋል። የተንቤን ህዝብም\nብልሹ የአስተዳደር ጥያቄዎች\nእንዲፈቱ በተደጋጋሚ ሰልፍ\nወጥቷል ያሉት አቶ ገብሩ፤\nበእንደርታ ውስጥ የመሬት\nዝርፍያን የተቃወሙ ገበሬዎች\nአሸባሪ ተብለውና ህገመንግስቱን\nንደዋል በሚል መታሰራቸውን\nአስታውሰዋል። አዲስ ዘመን ግንቦት 30/2011ምህረት ሞገስ ", "passage_id": "8889219ebc7883cf8163d765fd0860f2" }, { "passage": "ቢቢሲ፡ አሁን በኢትዮጵያ ባለው ለውጥ ላይ ህወሓት እንደ እንቅፋት ተደርጎ ይቀርባል። ለውጡን እንዴት ያዩታል ? \n\nአቶ አባይ ፀሐዬ፡ አሁን በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ለውጥ ኢህአዴግ 'ብዙ በድያለሁ፤ አጥፍቻለሁ' ብለው አራቱ አባል ድርጅቶች ገምግመው ሕዝብን ይቅርታ ጠይቀው የተጀመረ ነው። ኢህአዴግ በዚህ ደረጃ እራሱን እንዲፈትሽ፣ መፈትሄ እንዲያሰቀምጥና ሕዝብን ይቅርታ እንዲጠይቅ ህወሓት የጎላ ድርሻ ተጫውቷል። \n\nየህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ግምገማ በጣም ጥልቀትና ስፋት ነበረው። ሌሎችም እንደ ፈር ቀዳጅና እንደ ማሳያ ነው የወሰዱት። ስለዚህ ህወሓት የለውጥ ጀማሪ፣ በለውጡ የነቃ ተሳትፎና አብነታዊ ሚና ተጫውቷል። ከዚያ በፊት ህወሓት በትግራይ ሕዝብ ተዓማኒነት እስኪያጣ ድረስ የከፋ ችግር ነበረበት፤ በአገር ደረጃም የኢህአዴግ አካል ሆኖ ብዙ ስህተት የፈፀመ ድርጅት ነው። ስለዚህ ስህተት አልፈፀምኩም፣ ጉድለት የለኝም፣ ያልተገባ ነገር አልሠራሁም አላለም። ይሄን ሁሉ ዘርዝሮ ለኢህአዴግ አቅርቧል፤ ለሕዝቡም ይፋ አድርጓል። \n\nከዚያ በኋላም ህወሓት የኢህአዴግ አካል ሆኖ ለተሠሩ ስህተቶችም ከግምገማና ከሂስ አልፎ ዶክተር ዐብይ ሊቀመንበርና ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ ሲመረጥ፤ በጋራ የመረጥነውን መሪ በፀጋ ተቀብሎ ደግፏል። በፓርላማም ድምፁን ሰጥቶ 'የጋራ መሪያችን ነው፤ የጋራ ለውጥ ነው' ብሎ በቅንነት በሕግ አክባሪነት ለውጡን ደግፏል። \n\n• አቶ ጌታቸው አሰፋ የት ናቸው? የእስር ትዕዛዝ ወጥቶባቸዋል?\n\n• በሱዳን ሄሊኮፕተር ተከስክሶ አራት ባለሥልጣናትን ገደለ \n\nበተሠሩ መልካም ሥራዎች ላይም ህወሓት ጉልህ ሚና ነበረው። ለምሳሌ ከኤርተራ ጋር የተደረገው የሰላም ስምምነት፣ በውጭ የነበሩ ተቃዋሚዎች እንዲመጡ፣ በነፍጥ ሲፋለሙ የነበሩ ወደ ሰላም እንዲመጡ የተደረገው ጥረት መነሻው የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚና የኢህኣዴግ ምክር-ቤት ውሳኔ ነው። \n\nአፈፃፀሙ ላይ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዶክተር ዐብይ ላቅ ያለ ጥረት አድርገው ውጤታማ እንዲሆን ሠርተዋል። ይህንንም ህወሓት አድንቆና አመስግኖ ተቀብሎታል። ከዚያም አልፎ የእሰረኞችን መፍታት አድንቆና ተቀብሎ ነው የሄደው። \n\nእንዲሁም የባለስልጣናት ሽግሽግ ሲደረግ፤ በርካታ ከስልጣንና ከሚኒስትርነትም የተነሱ ሰዎች ፣ ከዚያ በታች ባሉ የሲቪል ኃላፊነት ቦታዎችም፣ ከሠራዊትም በርካቶች ከህወሓት ነው የተነሱት። ይሄንንም በፀጋ ነው የተቀበለው። ዲሞክራሲያዊ ነን በሚሉ ሃገራት አንድ ፓርቲና አንድ ግለሰብ ከሠራዊት ወይም ከድህንነት ኃላፊነት ሲነሳ ስንት ኩርፍያና ግርግር ይፈጠራል። ህወሓት ግን አካሄዱ ላይ ይስተካከል ብሎ አስተያየት ሰጥቷል፤ ነገር ግን ተግባራዊ አድርጎታል። የቱ ጋር ነው ለውጡን የተቃወመው?\n\nአፈፃፀም ላይ የታዩ ጉድለቶች ነበሩ እነርሱም ደግሞ ይታረሙ ብሏል። ያለፉትን 27 ዓመታት ምንም እንዳልተሠራ ይነገራል \"ይሄ ትክክል አይደለም፤ አብረን ነው የሠራነው\" በሎ ሃሳብ አቅረቧል። እንዴ ህወሓት ነው እንዴ የሰራው? ህወሓት ብቻ ነው እንዴ የሚከፋው? ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብም'ኮ የለፋበት ነው። ይሄ ሲነቋሸሽ ህወሓትና የትግራይ ሕዝብ ልዩ ቅሬታ፣ ልዩ መከፋት የሚሰማቸው መስሎ የሚታያቸው ካሉ ትክክል አይደሉም። ይሄ ሚዛኑን ይጠብቅ ማለት ለውጥ መቃወም አይደለም። \n\nቢቢሲ፡ ለምሳሌ የኢትዮ-ኤርትራ ጉዳይ ላይ ህወሓት ተቃውሞ አሰምቶ ነበር ...\n\nአቶ አባይ ፀሐዬ፡ የኢትዮ-ኤርትራ ሰላም አፈፃፀሙ ላይ የተወሰኑ ጉድለቶች ነበሩ። ሕዝብን ብናማክር ይጠቅም ነበር። በትግራይ በኩል ያለው በር ይከፈት፤ ግንኙነቱ ከአዲስ አበባ ብቻ አይሁን፤ አሰብ ብቻ ሳይሆን ምፅዋም ይከፈት። የትግራይ ድንበሮች ክፍት ይሁኑ የሚል ነው። ይህንን ሃሳብ ማቅረብ ለውጡን መቃወም... ", "passage_id": "75a068f27210c4239171e5996d14a0ba" }, { "passage": "በትጥቅ ትግሉ ወቅት ስለነበራቸው ሚና እንዲሁም ስለወቅታዊ የኢትዮጵያ የፖለቲካዊ ሁኔታ ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር ቆይታ አድርገዋል።\n\nቢቢሲ፡ ህወሓት ከተመሠረተበት ግዜ አንስቶ በክብር እስከተሰናበቱበት ድረስ አመራር ላይ ነበሩ። ከልምድዎ እጅግ የሚኮሩበት ወይም እንዲህ ባደርግ ኑሮ ብለው በግል ወይም እንደ ድርጅት የሚቆጩበት ነገር አለ?\n\nአቦይ ስብሃት፡ እንደ ድርጅት ድክመት አልነበረብንም አልልም፤ ብዙ ድክመቶች ነበሩብን። በግልም ስህተቶችን አልፈፀምንም አልልም። \n\nእኔም በግሌ አንዳንድ ስህተቶችን ፈጽሜያለሁ፤ ሆኖም በቅጽበት ይታረም ነበር። የሓኽፈን ውጊያ የኔ ስህተት ነበር ውጊያው ድል አልነበረም። ግን በፍጥነት ተምረን በፍጥነት ነበር የምናርመው። \n\nከድክመት እንማር ነበር፤ በድልም የመርካት ሁኔታ እንዳይኖር እንማርበት ነበር። በድል መስከር አይገባም። የኢትዮጵያ መጻኢ ታሪክ ተጽፏል፤ ፕሮግራም ላይ ሰፍሯል። ከዚሁ በመነሳት ነው 'ትግሉ ረጅምና መራራ ነው፤ ድል ግን አይቀሬ ነው' ነው የተባለው።\n\n• ህወሓት: \"እሳትና ጭድ የሆኑ ፓርቲዎች ሊዋሃዱ አይችሉም\" \n\nቢቢሲ፡ ሥልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ሥርዓቱ በሙስና በስብሷል ይሉ ነበር። እርስዎና ቤተሰብዎ ግን በሙስና ትታማላችሁ ምን አስተያየት አለዎት?\n\nአቦይ ስብሃት፡ ሙስና ቀስ እያለ የሚመጣ ችግር ነው። ሙስና አለ በሚለው ላይ 'መጠኑ ትንሽ ነው፤ አይደለም መጠነ ሰፊ ነው' የሚል ክርክር ነበር። ይብዛም ይነስም ምልክቱ ሲታይ ቶሎ መታረም ነበረበት። ኋላ ላይ እያደገ መጥቶ ሙስናን መጸየፍ እየደከመ መጣ።\n\nሙስና የሥርዓታችን ዋነኛው ጠላት ነው እየተባለም ጥንቃቄያችን ግን እየቀነሰ መጣ። በ2008 እናጽዳው ተብሎ ታወጀ። ጸረ ዴሞክራሲያዊ ጠባብ ብሔረተኝነት (ጠባብነትና ትምክህት ማለት ነው)፣ የሃይማኖት አክራሪነት ጠላቶቻችን ናቸው ብለን ለይተን አስቀመጥን። \n\nዋናው ተጠያቂ ደግሞ የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ነው፤ በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ምክትሉ ናቸው ብለን አስቀመጥን። ስለዚህ በፍጥነት መታደስ አለብን ብለን ወሰንን። ዶክተር ዐብይ ከተመረጠ በኋላም አሁንም በፍጥነትና በጥልቀት መታደስ አለብን ካልሆነ ኢትዮጵያ አደጋ ውስጥ ነው ያለችው አልን።\n\nይህ ሳይተገበር ቀረ፤ እንዴት ቀረ? ማን አስቀረው? ተአምር ነው። \n\nአንድን ነገር ሊሆን አይገባውም ካላልክ በስተቀር ይለመዳላ፤ አሁን እየተለመደ ነው። ይህ ጉዳይ እንዴት ጠፋ ስትል፤ እኔ ጠፍታ ዳናዋ ካልተገኘው የማሌዥያ አውሮፕላን ጋር ነው የማመሳስለው።\n\nቢቢሲ፡ እርስዎን በተመለከተ ሰለሚነገረውስ? \n\nአቦይ ስብሃት፡ የዚያው አካል ነው። መጣራት አለበት እሱ እንዲሆን እኮ ነው እየተጠየቀ ያለው። ሙሰኛ ማነው? አቶ እገሌ ወይስ ወይዘሮ እገሊት? ደፍሮ የሚያወጣው ነው የታጣው። ወኔ የለም፤ ድፍረት እኮ ነው የታጣው። \n\nየአገር ውስጥ ሙያተኞች ከውጭ ባለሞያዎች ጋር ሆነው እንዲሠሩ 'ፕሮፖዛል' ለአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ ደመቀ መኰንንና አቶ አባይ ወልዱ ቀርቦ ነበር። እንገባበታለን ተብሎ ቀረ።\n\nነጻና ገለልተኛ በሆነ አካል መጣራት ነበረበት። አንተስ ብትለኝ እዚያው ውስጥ መጣራት አለብኝ።\n\n• \"ለስልጣን ተብሎ የሚፈጠር ውህደትን ህወሓት ፈጽሞ አይቀበለውም\" አቶ ጌታቸው ረዳ \n\nቢቢሲ፡ አቦይ ስብሃት በአሁኑ ሰዓት ምን ዓይነት ሚናና ኃላፊነት አለዎት?\n\nአቦይ ስብሃት፡ የእኔ እምነት የህወሓት/ኢህአዴግ ፖለቲካዊ ፕሮግራም ነው። አሁን አለ ወይስ የለም የሚለውን ቆይቼ እገልጸዋለሁ። በግል የህወሓት ደጋፊ ነኝ። ትግራይ ውስጥ ትግራይን፤ ከትግራይ ደግሞ ለኢትዮጵያ፤ ህወሓትን የሚተካ የፖለቲካ ኃይል የለም።\n\nበመተዳደሪያ ሕጉ መሰረት [የህወሓት] አባል አይደለሁም። እየተናገርኩ ያለሁትም ህወሓትን... ", "passage_id": "c590b94cc04a6cf2a20fec0c67ea7d0c" } ]
33a27a3da597d9efdadc3b586099f1c1
6759fcc5762fa5dd8affae6524dd8f39
ባየር ሙኒክ በኢትዮጵያ ሥልጠና ይሰጣል
 የጀርመኑ ኃያል ክለብ ባየር ሙኒክ በኢትዮጵያ ለክለቦች የተለያዩ ሥልጠናዎችን እንደሚሰጥ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡ ሥልጠናው ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ባለሙያዎቹም ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከጀርመኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ጋር የተለያዩ ሥራዎችን በጋራ ለማከናወን ማቀዱ ይታወቃል፡፡ ይህንን ተከትሎም ከዚህ ቀደም የልምድ ልውውጥና ሥልጠናዎችን ሰጥቷል፡፡ አሁንም ከፌዴሬሽኑ የቴክኒክና ልማት ዳይሬክተር ጋር ባደረገው ቅድመ ዝግጅት፤ ለወጣት አሰልጣኞች ለ15 ቀናት የሚቆይ ሥልጠና የሚሰጥ መሆኑን ፌዴሬሽኑ በድረ ገጹ አስነብቧል፡፡ ሥልጠናውን የሚሰጡት ባለሙያዎች ትናንት አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን ለቀጣይ 15 ቀናትም ቆይታ የሚያደርጉ ይሆናል፡፡ ሥልጠናው የሚካሄደው በሁለት ዙር ሲሆን፤ የመጀመሪያው ዙር ሰልጣኞች ከየክልሉ የተውጣጡ ወጣትና ጀማሪ አሰልጣኞች ናቸው፡፡ ወጣቶቹ ከዚህ ቀደም በተሰጠው ሥልጠና ተገቢውን ውጤት በማሟላት ለቀጣይ ያለፉ 30 አሰልጣኞች ሲሆኑ፤ ለተከታታይ አምስት ቀናት በሥልጠና ላይ የሚቆዩም ይሆናል፡፡ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚሰጠው ሥልጠናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 13/2012 ዓ.ም የሚቆይ መሆኑም በዘገባው ተመላክቷል፡፡ሁለተኛው ዙር ሥልጠናም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወንድ ክለብ አሰልጣኞችንና አንደኛ ዲቪዚዮን ሴቶች ፕሪሚየርሊግ ክለብ አሰልጣኞችን የሚያካትት ነው፡፡ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠናው ከየካቲት 16-18/2012 ዓ.ም ለሦስት ቀናት የሚሰጥም ይሆናል፡፡ ቀጣዩ መርሃ ግብርም ክለቡ በሚያዘጋጀው የባየር ሙኒክ የወጣቶች ዋንጫ ላይ ተሳታፊ ሊሆኑ የሚችሉ ከ15 ዓመት በታች ታዳጊዎችን መመልመል ነው፡፡ የሚመለመሉት አስር ተጫዋቾችም በሚያዝያ ወር መጨረሻ በጀርመን የሙኒክ ከተማ በሚካሄደው የባየርሙኒክ ዋንጫ ውድድር ላይ ተሳታፊ የሚሆኑበትን ዕድል የሚያመቻች መሆኑንም በዘገባው ተጠቁሟል፡፡ አዲስ ዘመን የካቲት 9/ 2012 ዓ.ም ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27414
[ { "passage": "የጀርመኑ ኃያል ክለብ ባየርን ሙኒክ የክብር አምባሳደር እና አመራሮች ከፊታችን እሁድ ጀምሮ አዲስ አበባ ይገባሉ።የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽና እና የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን በጋራ በመሆን ባመቻቹት ዕድል መሰረት የባየርን ሙኒክ የክብር አምባሳደር የሆነው ብራዚሊዊው የቀድሞ የክለቡ አጥቂ ጂኦቫኒ ኤልበር፣ የክለቡ ዋና ስራ አስፈፃሚ ካርል ሄይንዝ ሩሚኒገ እና ሌሎችም ግለሰቦች ጨምሮ ከፊታችን እሁድ ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ይሆናል።ለቀናት በአዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ የተለያዩ ተግባራት ያከናውናሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን በዋናነት በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር በሚካሄደው ከ17 ዓመት በታች ውድድር ተሳታፊ ከሆኑት ክለቦች መካከል ኢትዮጵያ መድን፣ ኢትዮጵያ ቡና፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሠላም፣ ኢ/ወ/ስ አካዳሚ እና ኢትዮ ኤሌትሪክ ጨምሮ የሰውነት ቢሻው አካዳሚ ቡድኖች እያንዳንዳቸው አስር አስር ተጫዋቾችን በመላክ የፊታችን ረቡዕ በአዲስ አበባ ስታዲየም በሚደረጉ ጨዋታዎች በኢትዮጵያ እግርኳስ ታዳጊዎች ላይ እየተሰራ ያለውን እንቅስቃሴ ከመገምገማቸው ባሻገር ጥሩ መንቀሳቀስ የቻሉትን ተጫዋቾች የተሻለ እድል የሚያገኙበትን መንገድ ያመቻቻሉ ተብሎ ይጠበቃል።ከዚህ በተጨማሪ የባየርሙኒክ የረጅም ዓመት ስፖንሰር የሆነው ታዋቂው የስፖርት ትጥቆች አምራች አዲዳስ በኢትዮጵያ ሊከፍተው ያሰበው እና በግንባታ ላይ የሚገኘውን የሽያጭ ማዕከል ከመጎብኘታቸው ባሻገር ኦሎምፒያ የሚገኘው የአዲዳስ ይፋዊ የምርት አከፋፋይ የሆነውን ድርጅት ማክሰኞ የሚዲያ አከላት በተገኙበት ጉብኝት ያደርጋሉ። ከጋዜጠኞች ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉም ተብሏል።የአምስት ጊዜ የአውሮፓ ቻምፒዮኖቹ አዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች ጋር በቀጣይ በሚኖረው ሁለተናዊ ግኑኝነት ዙርያ ውይይት ያደርጋሉ፤ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣሉም ተብሎ ይጠበቃል።የክለቡ ስራ አስፈፃሚ በመሆን እየሰሩ የሚገኙት ካርል ሄይንዝ ሩሚኒገ የቀድሞ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን እና ባየርን አጥቂ የነበሩ ሲሆን በ1980 እና 81 የባሎን ደ’ ኦር አሸናፊ ናቸው። ብራዚላዊው ጂኦቫኒ ኤልበር ደግሞ ከ1997 እስከ 2003 ለክለቡ የተጫወተ ስመጥር አጥቂ ነው።", "passage_id": "04d6e7bd1aa7b09e065a450d349c97bb" }, { "passage": "የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን እና የእንግሊዙ እግር ኳስ ማኅበር (FA) ያዘጋጁት የአሰልጣኞች ስልጠና በአዲስ አበባ ስታዲየም በመስጠት ላይ ይገኛል።ስልጠናው የ36 የከፍተኛ ሊግ ዋና አሰልጣኞችን ያካተተ ሲሆን የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ቴክኒክ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር አቶ መኮንን ኩሩ መርሐ ግብሩን በንግግር ከፍተዋል። የስልጠናው ዓላማ በእግርኳስ የጨዋታ እቅድ እንዴት ማውጣት እንዴት እንደሚቻልና ወጥነት ያለው የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ መፍጠር ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል። ስልጠናውን በሁለት ባለሞያዎች እንደሚሰጥም ማወቅ ተችሏል።ስልጠናው በሁለት መርሀ ግብር የተከፈለ ሲሆን በጠዋት መርሀ ግብር የክፍል ውስጥ ትምህርት፤ በከሰዓቱ ደግሞ የሜዳ ላይ ተግባር የሚከናወን ይሆናል።ለአምስት ቀን የሚቆየው ይህ ስልጠና በመጪው ዓርብ ሲጠናቀቅ ትናንት በነበረው የከሰዓት መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ ጂራ በመገኘት ተከታትለዋል።", "passage_id": "b91047c6489debaf770cdb10e0bdf295" }, { "passage": "– የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን አካዳሚ የሚሰጠውን ሥልጠናውን ለሌሎች የአፍሪካ አገሮች ለመስጠት ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት ላይ መሆኑን አስታወቀ። አካዳሚው የሥልጠና አቅሙን አሁን ካለበት በአራት እጥፍ ለማሳደግ አቅዷል።255ሰልጣኞችንም ትናንት አስመርቋል። የአካዳሚው ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል አሰፋ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስረዱት አካዳሚው በአህጉሪቱ ያለውን ተቀባይነት መነሻ በማድረግ የሥልጠና አድማሱን እያሰፋና የሌሎች አፍሪካ አገሮችን ጥያቄዎች ለማሟላት ጥረት እያደረገ ነው። በአብራሪነት፣በአስተናጋጅነት፣በአውሮፕላን ጥገና ቴክኒያሽንነትና በሽያጭ ባለሙያነት አካዳሚው የሚሰጣቸው ሥልጠናዎች ተቀባይነታቸው እያደገ መምጣቱንም አብራርተዋል።አካዳሚው የአገር ውስጥ የሥልጠና አቅምን ለማሳደግ ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ እያደገ የመጣውን የአየር መንገዱን ተደራሽነት በመጠቀም ከሌሎች አገሮች ሰልጣኞችን እየተቀበለ ለማሰልጠን ትኩረት መስጠቱንም ተናግረዋል። በዚህም በዚህ ዓመት ከሞዛምቢክ፣ከናሚቢያ፣ከናይጄሪያና ከኢኳቶሪያል ጊኒና ከሌሎች አገሮች የመጡት ሰልጣኞች ሥልጠናውን በመከታተል ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል።ከመካከላቸው አምስት የሞዛምቢክ ሴት ፓይለቶች በቅርቡ መመረቃቸውንም አስታውሰዋል። አካዳሚው ቀደም ሲል በዓመት ከ250 የማይበልጠውን የሰልጣኞች ቁጥር ዘንድሮ አንድ ሺህ ማድረሱንም አቶ ሳሙኤል አመልክተዋል። ለዚህም እንዲረዳው አካዳሚውን በመማሪያና በአስተዳደር ክፍሎችና በመሣሪያዎች የማሟላትና ሥርዓተ ትምህርቱን የመከለስ ሥራዎች በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በተጨማሪም በኮሜርሻል አብራሪዎች፣በአመራርና በማርኬቴንግ ዘርፎች የሚያሰለጥንበት ማዕከል ለማቋቋም ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። በአየር መንገዱ የተያዘውን ራዕይ 2025 ለማሳካትም የሥልጠና ቅበላ አቅሙን አራት ሺህ ለማድረስ የተጠናከረ እንቅስቃሴ እንደሚያደርግም ገልጸዋል። አየር መንገዱ እስከ ሁለት ዓመታት በሚቆይ ሥልጠና በአስተናጋጅነት፣በቴክኒሽያንነትና በሽያጭ ሠራተኝነት ያሰለጠናቸውን 255 ባለሙያዎች ትናንት አስመርቋል። የአየር መንገዱ የበረራ ክፍል ዋና ኃላፊ አቶ መስፍን ጣሰው ለተመራቂዎቹ የበረራ ክንፍና ዲፕሎማ እንዲሁም በሥልጠናቸው ብልጫ ላመጡት ደግሞ ዋንጫና የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል።ከሰልጣኞቹ 71ዱ አስተናጋጆች ናቸው። ከሰልጣኞቹ አንዱ ከኢኳቶሪያል ጊኒ የመጣ ነው። አየር መንገዱ በግማሽ ክፍለ ዘመን የሥልጠና ዕድሜው በአፍሪካና ከመካከለኛው ምሥራቅ ለሚገኙ 40 አገሮች ለተውጣጡ ሥልጠና ሰጥቷል። አካዳሚው እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1957 ከተመሰረተ ጀምሮ ከስምንት ሺህ በላይ ሰልጣኞችንም ማስመረቁን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በዘገባው አመልክቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ቀዳሚ ከሚባሉት አየር መንገዶች ተርታ የተሰለፈ አገር በቀል ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል። ", "passage_id": "4ca498d9eca2e42e7f80321ee8849123" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- መለስ ፋውንዴሽን ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ በሒሳብና በፊዚክስ ትምህርቶች የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ 170 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የቴክኖሎጂ ሥልጠና ሰጠ። በፋውንዴሽኑ የኢኮሎጂ ኃላፊ ወይዘሮ ሰምሀር ሲሳይ ፋውንዴሽኑ ለሁለተኛ\nጊዜ ባዘጋጀው የስልጠና መድረክ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት፣ የቴክኖሎጂ ሥልጠናው በኢኖቪሽንና ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰጥ\nነው። ተማሪዎቹ ከልጅነታቸው ጀምሮ የቴክኖሎጂ ፍላጎቱ እንዲያድርባቸው ከማድረጉም በላይ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች በሚገቡበት ወቅት ሳይንሱን\nመርጠው ወደ አዳዲስ ነገሮች ፈጠራ እንዲያዘነብሉ ይረዳቸዋል ብለዋል። ወጣት ተማሪዎቹን ከቴክኖሎጂዎች ጋር የማስተዋወቁና ፍላጎቱን የማስረጽ\nሥልጠናው እየተሰጠ የሚገኘው ዘንድሮ ለሁለተኛ ዙር ሲሆን እስከ አራተኛ ዙር በየክረምቱ የሚቀጥልም ሆኖ ለአንድ ወር ያህል ጊዜ\nየሚወስድ ነው ብለዋል። ተማሪዎች ስለ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ከዚያም በተጨማሪ ሳይንስ፣ሒሳብ\nእና ኢንጂነሪንግ ዘርፎች ላይ ትኩረት እንዲሰጡ ታስቦ የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን የተናገሩት ወይዘሮ ሰምሀር፣ በሥልጠናው መጨረሻም\nተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታዎቻቸው አዳዲስ ሐሳቦች አፍልቀው በተግባር ወደ ውጤት የሚቀይሩበት እድልና አሰራር እንደሚመቻችላቸው\nጠቁመዋል። ከኦሮሚያ ልዩ ዞን ለገጣፎ የመጣው ተማሪ ምህረትአብ ሳምሶን እንደተናገረው፣\nሥልጠናው የኮምፒዩተር ሳይንስ ሲሆን በቀጣዮቹ ጊዜያት የቴክኖሎጂ ፍላጎት እንዲያድርብን የሚያደርግ ነው ብሏል። ዓለም የምትመራው\nበቴክኖሎጂ ስለሆነ በየትኛውም ዘርፍ የዚህ እውቀት ባለቤት ሆኖ መገኘት አስፈላጊና ተመራጭ ሊያደርግ እንደሚችል ጠቅሶ የተማሪዎችን\nየቴክኖሎጂ እይታም የሚያሳፋ እንደሆነ ተናግሯል። የኮምፒዩተር ፕሮግራም ሥልጠናው ሀገሪቱን የሚረከቧት ወጣቶች የቴክኖሎጂ እውቀቱ ያላቸው  እንዲሆኑ በር ይከፍታል የምትለው የመቐለዋ ተማሪ ሊዲያ ጸጋነህ በቀጣይ የዩኒቨርሲቲ\nትምህርቴን በሕክምናው ዘርፍ የመማር እቅድና ፍላጎት ቢኖረኝም የቴክኖሎጂ እውቀቴን ማጎልበቴ ለሀገሬ በሙያዬ አዲስ ነገር ማበርከት\nእንድችል ያደርገኛል ብላለች። ከጎንደር የመጣችው ተማሪ ቃልኪዳን ኃይሉ በበኩሏ የኮምፒዩተር\nቴክኖሎጂ ሥልጠናው ለማንኛውም ሰው በዚህ ዘመን ያለው ፋይዳ አያጠያይቅም። ለተማሪዎች ሲሆን ደግሞ ጥቅሙ እጥፍ ድርብ ይሆናል፣ምክንያቱም\nከዓለም ጋር በቅርበት በመተዋወቅ ለሀገራችን አዳዲስ ፈጠራዎች ማበርከትና ትውልዱን ለማስተማር ሰፊ እድል ባለቤቶች ነን ስትል ተናግራለች።አዲስ ዘመን ነሐሴ 16/2011ሙሐመድ ሁሴን", "passage_id": "b2363429e4b3b47fba2303fe2c698f84" }, { "passage": "የለውጥ አመራር ሰጭነት ስልጠና በባሕር ዳር እየተሰጠ ነው፡፡ለክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ራሳቸውን አውቀው ለሌሎች መንገድ እንዲያሳዩ የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ለአማራ ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚቆይ የአሻጋሪ አመራር ሰጭነት (ትራንስፎርሜሽናል ሊደርሽፕ) ስልጠና በባሕር ዳር ከተማ እየተሰጠ ነው፡፡የስልጠናው ዓላማ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቅማቸውን ፈትሸው ስለተቋማዊ ዕድገት እና ተግባቦት ክህሎት ግንዛቤ መፍጠር ነው፡፡ ልማትን፣ ሠላምን እና አብሮነትን በማስጠበቅ የኢትዮጵያን መፃዒ ዕድል የተሻለ ለማድረግ በሚመሩት ሕዝብና ሠራተኞች መካከል መነቃቃት እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡በሀገሪቱ ከዘመናት በፊት የነበረው አንድነት እና መተሳሰብ እየቀነሰ መምጣቱን ተከትሎ በስልጠና የመሪዎችን የአዕምሮ ውቅር ማስተካከል ተገቢ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር በዛብህ ገብረየስ ተናግረዋል፡፡በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አስተባባሪነት የሚሰጠውን ስልጠና ‹ጴጥሮስ ኔትወርክ› የሚባል በየአሜሪካን ድርጅት እና ‘ፎርድ ቴይለር ግሩፕ’ አማካኝነት የሚሰጥ ነው፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት እየተቀነቀነ ያለውን አሻጋሪ አመራር ሰጭነት (ትራንስፎርሜሽናል ሊደርሽፕ) ጸሐፊ እና መሥራች ፎርድ ቴይለር ስልጠናውን ይሰጣሉ፡፡", "passage_id": "4e9ab045918276fd8321f98f70e00ecb" } ]
8e6167f0783d82e9bd6068262e8fe0df
b91076268f89ce5d1de2ac6ab4f9b259
ለኦሊምፒክ ዝግጅት አትሌቶች በከፍተኛ ደመወዝ ወደ ልምምድ ይገባሉ
እአአ የ1964ቱ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያ በታሪኳ ተሳታፊ የሆነችበት ሶስተኛው ኦሊምፒክ ነው። ታላቁ አትሌት አበበ ቢቂላ በኦሊምፒክ ማራቶን ለራሱ እና ለአገሩ ሁለተኛውን፣ በውድድሩ ደግሞ ብቸኛውን ሜዳሊያ ያገኘበትም ነበር። አሁን ደግሞ ጃፓን ከሃምሳ ስድስት ዓመታት በኋላ ኦሊምፒክን በምድሯ ለማስተናገድ ወራት ብቻ የቀሩበት ጊዜ ላይ እንገኛለን። በዚህ ታላቅ የስፖርት መድረክም የተሻለ ታሪክ ለማስመዝገብ ኢትዮጵያ በተለየ ትኩረት በመንቀሳቀስ ላይ ትገኛለች። በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ ከውጤታማነት ባሻገር ተሳትፎም ክብርን ያስገኛል። በውጤታማነት ድርብ ክብርን ለመጎናጸፍ ደግሞ ትኩረት፣ ጥረትና ጽናት አስፈላጊ መሆናቸው ይታመናል።በኦሊምፒክ መድረክ የአገሪቷን ስም በተደጋጋሚ ያስጠራው እንዲሁም ከፍተኛውን የውጤታማነት ስፍራ የሚይዘው የአትሌቲክስ ስፖርት ነው። ኢትዮጵያ ደግሞ በዚህ ስፖርት በተመዘገቡ ሜዳሊያዎች አማካኝነት ከውጤታማዎቹ አገራት መካከል 36ኛ ስፍራ ላይ ትገኛለች። ነገር ግን በዚህ መድረክ ውጤታማ ያደረጓት አትሌቶች የኋላ ታሪክ ቢጠና በግላቸው የሚያደርጉት ጥረትና ጽናት ሰፊውን ድርሻ ይይዛል። በመሆኑም መንግስት የተሻለ ትኩረት በመስጠት ውጤታማነቱን ለማሳደግና ለማገዝ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አስታውቋል። ለዚህም የመጀመሪያው ርምጃ አትሌቶች የዝግጅት ጊዜያቸውን በትኩረት እንዲያሳልፉ በተሻለ ስፍራ እንዲያርፉ ማድረግ ነው። በመሆኑም የዝግጅት ኮሚቴው ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጋር ባደረጉት ውይይት ለውድድሩ የተመረጡ አትሌቶች ካምፓቸውን ከፍተኛ ደረጃ ካላቸው ሆቴሎች መካከል በአንዱ እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተሰጥቷል። በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጥሪ የተደረገላቸው አትሌቶች ተሰባስበው ወደ ልምምድ እንደሚገቡ ተገልጿል። ከዚህ ቀደም በብሄራዊ ቡድን የታቀፉ አትሌቶች የላብ መተኪያ ወጪ እጅግ አናሳ መሆኑ በቅሬታ መልክ የሚነሳ ነበር። ይህንንም ለመቅረፍ በመንግስት በኩል በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ለታዋቂ አትሌቶች 50ሺ ብር ደሞዝ እንዲያገኙ እንዲሁም ለሌሎች ጀማሪ አትሌቶች 10ሺ ብር በየወሩ የሚከፈላቸው ይሆናል። በልምምድ ግብዓት እንዲሁም ትጥቅ በኩልም ችግር እንዳይገጥማቸው እየተሰራ መሆኑም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ከትናንት በስቲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጧል። ዝግጅቱን በበላይነት የሚመራው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከስፖርት ማህበራትና ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በመሆን ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ዝግጅ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። ለዝግጅቱም የቶኪዮ ብሄራዊ ዝግጅት ኮሚቴ እንዲሁም የቶኪዮ ኦሊምፒክ ቴክኒክ ኮሚቴ በሚልም ሁለት ኮሚቴዎችን አዋቅሯል። ብሄራዊ ኮሚቴው በቀድሞ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ የሚመራ ሲሆን፣ ትኩረቱን በሃብት አሰባሰብ፣ የልማት ስራዎች፣ የደጋፊ አባላት ላይ እንዲሁም በስፖርተኞች ሽኝትና አቀባበል ላይ ያደርጋል። በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጂሎ የሚመራው የቴክኒክ ኮሚቴው ደግሞ ከተለያዩ ባለሙያዎች ጋር በመሆን በአትሌቶችና አሰልጣኞቻቸው ምርጫ ላይ የሚሰራ ይሆናል። በዚህም መሰረት አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እጩ አትሌቶችንና አሰልጣኞቻቸውን ከቀናት በፊት አሳውቋል። በማጣሪያ ውድድር ላይ ያሉት የቦክስና ወርልድ ቴኳንዶ ስፖርቶችን ጨምሮ ከውሃ ስፖርቶችና ብስክሌት ፌዴሬሽኖችም ጋር ኮሚቴው በትብብር በመስራት ላይ ይገኛል። ቀደም ብሎ ወደ ዝግጅት ምዕራፍ በመግባት ላይ የሚገኘው የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በበኩሉ 90 አትሌቶችንና 15 አሰልጣኞችን በማጨት ወደ ልምምድ ለመግባት በመንደርደር ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል። ብሄራዊ ቡድኑ በሶስት ምዕራፍ የተከፈለ ዝግጅት የሚያደርግ ሲሆን፤ በመጨረሻም 50 አትሌቶች ወደ ቶኪዮ የሚጓዙ ይሆናል። ለጊዜው በተሳትፎ ደረጃ የተያዘው ከ800ሜትር እስከ እርምጃ ባሉት ርቀቶች ቢሆንም ሚኒማውን ማሟላት ከተቻለ በ400ሜትርም ተሳታፊ የመሆን እድል እንደሚኖር ተጠቁሟል።የቴክኒክ ኮሚቴው ቀድሞ ዝርዝራቸው ይፋ የተደረጉትን አሰልጣኞች የተመረጡበት መስፈርትም በርካታ አትሌቶችን በማስመረጥ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ውድድሮች ባላቸው ልምድ መሆኑን ገልጿል። የአትሌቶች የምርጫ መስፈርት ደግሞ እአአ በ2019 ባስመዘገቡት ሰዓት መሰረት በመምረጥ በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የጸደቀ መሆኑ ተብራርቷል። ለኦሊምፒክ የሚደረገው ዝግጅት አገርን ለማስጠራት የሚደረግ እንደመሆኑ በሁሉም አካላት ዘንድ በተለይም በአትሌቲክስ ፌዴሬሽንና ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች በኩል ያለው አለመግባባትን ከወደ ጎን በመተው ለውጤታማነት በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑ በመግለጫው ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን አርብ የካቲት 13/2012ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27626
[ { "passage": "የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በቶኪዮ ለሚዘጋጀው የ2020 የኦሊምፒክ ውድድር ለማለፍ የቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታውን ነገ ያከናውናሉ።በ2020 ጃፓን ቶኪዮ ላይ ለሚደረገው የኦሊምፒክ ውድድር ለመሳተፍ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ እያደረጉ የሚገኙት የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን የመልስ ጨዋታቸውን ለማድረግ ካሜሩን ገብተዋል። ከሳምንት በፊት ባህር ዳር ላይ የተጫወቱት ሉሲዎቹ በተቀዛቀዘ የጨዋታ እንቅስቃሴ 1-1 መለያየታቸው ይታወሳል። 29 የልዑካን ቡድን ይዘው ከትላንት በስቲያ ወደ ካሜሩን ያመሩት ሉሲዎቹ ዛሬ ከሰዓት ጨዋታቸውን ነገ በሚያደርጉበት ኦምኒ ስፖርት ስታዲየም ልምምዳቸውን ሰርተዋል።በነገው ጨዋታ ማሸነፍ አልያም ከሁለት ጎል በላይ አቻ መውጣት ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያሳልፋቸው ሉሲዎቹ ከተጋጣሚያቸው ካሜሩን ብርቱ ፉክክር እንደሚጠብቃቸው ይገመታል። ከናይጀሪያ በመቀጠል ከአፍሪካ ሁለተኛዋ ሃያል ቡድን የሆነችው ካሜሩን በመጀመሪያው ጨዋታ (ባህር ዳር ላይ የተደረገው) ያልተሰለፉ ወሳኝ ተጨዋቾቿን በነገው ጨዋታ እንደምትጠቀምም ተሰምቷል።ጨዋታው ነገ 11:30 በኦምኒ ስፖርት ስታዲየም ይከናወናል።", "passage_id": "a1162009b5bb0d297b0943aad5df04c0" }, { "passage": " የዓለማችን ኮከብ አትሌቶች በዚህ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) በተስፋፋበት ወቅት በምን ሁኔታ ቀናቸውን እያሳለፉ እንደሚገኙ የስፖርቱን ዓለም ሰዎችና ሌላውን ማህበረሰብ ከማስተማር አኳያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን እያገኘ መሆኑ ይስተዋላል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን የአትሌቲክስ የጀርባ አጥንት የሆኑትና አትሌቶችን ላሉበት ደረጃ ትልቅ ሚና የሚጫወቱት አሰልጣኞች ሥራቸውን በምን መልኩ እያከናወኑ እንደሚገኙ ከሥራቸውና ከቫይረሱ ባህሪ አኳያ ብዙዎች ጥያቄ ሲያነሱ ይስተዋላል፡፡ የዓለም አትሌቲክስም በድረ ገጹ በተለያዩ ዓለማት ቻምፒዮኖችን ያፈሩ አሰልጣኞች በዚህ ወቅት ሥራቸውን በምን መልኩ እየከወኑ እንደሚገኙ የተለያዩ ቅኝቶችን በማቅረብ ሌሎች እንዲማሩበት ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ \nበዓለም አትሌቲክስ ተሞክሯቸውን እንዲያጋሩ ከተመረጡት አሰልጣኞች መካከል አንዱ ደግሞ የዓለም ሁለተኛው የማራቶን ፈጣን ሰዓት ባለቤቱ ቀነኒሳ በቀለ አሰልጣኝ መርሻ አስራት ናቸው፡፡ አትሌቱ በሦስት ኦሊምፒኮች ተሳትፎው ወርቃማ ታሪክ እንዲጽፍ ከጀርባ በመሆን ከፍተኛውን ድርሻ የተጫወቱት አሰልጣኝ፣ በዚህ የውድድር ዓመት ኮከቡ አትሌት በለንደን ማራቶን የርቀቱን ክብረወሰን እንዲሁም በጃፓኗ ቶኪዮ ለማካሄድ በታሰበው ኦሊምፒክ በማራቶን አራተኛውን ድል ለማስመዝገብ ትልቅ ዝግጅት አድርገው ነበር፡፡ \nየኦሊምፒኩንና የተጠባቂውን ለንደን ማራቶን መራዘም ተከትሎም ቀነኒሳ ከምንጊዜም ተቀናቃኙና የወቅቱ የማራቶን የዓለም ባለ ክብረወሰን ከሆነው ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ጋር በተንቀሳሳሽ ምስል የታገዘ ውይይት ማድረጋቸውን ኤንኤን ትሬኒንግ የተባለው ድረገጽ አስመልክቷል፡፡ በዚህም አትሌቶቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በቤታቸው በመሆን የግል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሰልጣኞች ዓለም ውጥረት ውስጥ በገባበት በዚህ ወቅት ሥራቸውን በምን መልኩ ይከውናሉ፣ ቀናቸውንስ እንዴት ያሳልፉታል፣ አትሌቶች ከልምምድ እንዳይርቁና ብቃታቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ የአሰልጣኞቹ ሚና በምን መልኩ አትሌቶች ጋር እየደረሰ ይገኛል? ለሚለው የአምስትና አስር ሺ ሜትርን ክብረወሰን ለረጅም ዓመት ሳያስደፍር ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ አሰልጣኝ ተሞክሯቸውን ያጋራሉ፡፡ \nአሰልጣኝ መርሻ የመጀመሪያው ቁም ነገር ዓለም የገጠማትን ይህንን ወጀብ በምን መልኩ ማለፍ ይቻላል? የሚለውን ማሰብ ቀዳሚ እንደሆነ እምነታቸው ነው፡፡ ወረርሽኙ በውድድሮች ላይ እንዲሁም በቡድን በሚሰጡ\n ስልጠናዎች ላይ የራሱን አሉታዊ አስተዋፅዖ እንዳሳደረ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን ጊዜውን በጥንካሬ ማሳለፍ የግድ ነው ይላሉ፡፡ ሰልጣኞቻቸውም በዚህ መልክ መቆየት እንዳለባቸው ይጠቁማሉ፡፡ በንግግራቸውም ‹‹ሁሉም አትሌቶቼ ጠንካራና በባህሪያቸውም ለሌሎች ምሳሌ መሆን ይገባቸዋል፤ እንደ አሰልጣኝ የምነግራቸውም ይህ ጊዜ ያልፋል ብዬ ነው›› ብለዋል፡፡ \nምንም እንኳን በዚህ ወቅት ሁሉም ውድድሮች ከተያዘላቸው መርሐ ግብር ሽግሽግ እንዲደረግባቸውና ሌሎቹም የተሰረዙ ቢሆንም አትሌቶች ልምምዳቸውን ማቆም እንደማይገባቸው አሰልጣኝ መርሻ ይመክራሉ፡፡ አትሌቶች የሚሠሩት እንቅስቃሴም ለጥንካሬ እና አቅምን ለማዳበር የሚረዱ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ ይህንንም ሲያብራሩ ‹‹ለተወሰኑ ጊዜያት ውድድሮች ስለሌሉ ጠንክሮ መሥራት ተገቢ የሆነበት ወቅት ነው፡፡ በመሆኑም በእኔ ስር ለሚሰለጥኑ ሁሉም አትሌቶቼ መሥራት የሚገባቸውን እየጠቆምኳቸው ነው፡፡ ወቅቱ ጥንካሬን የሚያዳብሩበት ነው፤ በደንብ እንዲሠሩም ዕድል ይሰጣቸዋል›› ብለዋል፡፡\n ከዓለም አትሌቲክስ ጋር ቆይታ ያደረጉት ሌሎች አሰልጣኞችም በተመሳሳይ ለአትሌቶቻቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የማራቶንና ግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰን ባለቤቶቹ ኬንያዊን ኢሉድ ኪፕቾጌ እና ጆፈሪ ካምዎረር አሰልጣኝ ፓትሪክ ሳንግም ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡ በርካታ አትሌቶች በቡድን የሚያሰለጥኑት አትሌቱ ቡድናቸውን የበተኑት ከወር በፊትም ነበር፡፡ በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ታግዘው አትሌቶቻቸውን ቢያገኙም ለውጣቸውን የመመልከት ዕድል አለማግኘታቸው ፈተና እንደሆነባቸው ጠቁመዋል፡፡ \nብራዚላዊው አሰልጣኝ ሞራ ኮት አትሌቶች ቀድሞ በነበራቸው መነቃቃት ማቆየት አዳጋች መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ አሰልጣኞችና አትሌቶች መልካም መግባባት ያላቸው ከሆነም በሚያወጧቸው እቅድ መሰረት ባሉበት ሆነው በእንቅስቃሴ ላይ መቆየት ይችላሉ፡፡ ቢሆንም ይህ ጊዜ ሲያልፍ ምን ሊከሰት እንደሚችል ለመገመት አዳጋች መሆኑን አልሸሸጉም፡፡ ‹‹አዲስ ልምድ እንደምናገኝና ይህ\n ሁኔታ ለበጎ እንደሚሆንም ተስፋ አለኝ›› ይላሉ፡፡ \nየኒውዝላንድን አትሌቶች ሲያዘጋጁ የቆዩት አሰልጣኝ ዳሌ ስቴቨንሰን በበኩላቸው አትሌቶቻቸውን በስነልቦና እያገዙ እንደሚገኙና በቅርቡ ወደነበሩበት እንደሚመለሱ እየነገሯቸው መሆንኑን ገልጸዋል፡፡ ወቅቱ ወደኋላ የሚመለሱበት ሳይሆን በጥሩ ሞራል እንደ ሙሉ ጊዜ አትሌት ጊዜያቸውን መጠቀም እንዳለባቸውም ምክረሃሳብ ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኞችም አትሌቶቻቸው በምን መልኩ እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳለባቸው ማሳየት ተገቢ ነው የሚሉት አሰልጣኙ፤ በአንዳንድ አትሌቶቻቸው መደነቃቸውንም ይናገራሉ፡፡ አትሌቶች በአካባቢያቸው በሚያገኟቸው ቁሳቁስ ስልጠናቸውን እያደረጉ እንደሚገኙና በዚህም እንዲቀጥሉ አሳስበዋል:: ሌላኛው አሰልጣኝ ብራም ሶም አትሌቶች ከሁኔታዎች ጋር ራሳቸውን በማስማማት በዝግጅት ላይ መቆየት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡ ከአትሌቶች ጋር ፊት ለፊት በመተያየት ብቃታቸውን መገምገም ባይቻልም አዲስ ተሞክሮ እንዳስገኘላቸውም አክለዋል፡፡\nአዲስ ዘመን ሚያዝያ 28/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "d72f0cca261bbd4f4d28a62fa25e7ecb" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ከውድድር ውጪ ለሆኑ ብሔራዊ አትሌቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ተጠሪነቱ ምንም እንኳ ለሁሉም ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ቢሆንም፣ ብሔራዊ አትሌቶችን በሒደት ከገንዘብ ድጎማ ጀምሮ የተለያዩ ድጋፎችን ለማድረግ እየሠራ መሆኑ ፕሬዚዳንቱ ዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ አስታውቀዋል፡፡ ከድጋፉ ባሻገር የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (አይኦሲ) የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከመከሰቱ በፊት ለአገሮች በሰጠው ነፃ የትምህርት ዕድል ኮታ መሠረት ኤሊት አትሌቶች ዕድሉን እንዲጠቀሙ ለማድረግ ሥራዎችን እየሠራ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ ብሔራዊ ተቋማት ችግሩ በአትሌቶች ላይ ሥነ ልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና እንዳያሳድር የሚችሉትን እያደረጉ ይገኛሉ። ቀደም ሲል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት አትሌቶችንና መሰል ሙያተኞችን መደጎሙ አይዘነጋም፡፡ አዲስ ዘመን ሚያዝያ 27/2012 ", "passage_id": "982986101bc0dcb4fb98ac2c435347af" }, { "passage": "የዘንድሮው ዓመት የአትሌቲክስ አፍቃሪዎች ከዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ማግስት የታላቁን ስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ መዳረሻ በጉጉት የሚጠብቁበት በመሆኑ በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ የሚናፈቅ ነበር። የስፖርት ማህበራት የማጣሪያ ውድድሮችን በማካሄድ አገራትም ብሄራዊ ቡድኖቻቸውን በመመልመል ወደ ዝግጅት በመግባት ላይ እንደነበሩም ይታወሳል። ነገር ግን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ የዓለም ህዝብ ስጋት በመሆኑ ምክንያት ታላቁ ኦሊምፒክ ሊራዘም ችሏል። ከኦሊምፒኩ ጎን ለጎንም የበጋውን መግባት ተከትሎ በርካታ የግልና ዓለም አቀፍ ውድድሮችም የሚካሄዱበት ወቅት ቢሆንም በርካቶች በተመሳሳይ ምክንያት ተሰርዘዋል። \nኦሊምፒኩ ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሟል ይባል እንጂ ከሰሞኑ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ከዚያም በላይ ለሆነ ጊዜ ሊቆይ እንደሚችልና ከነጭራሹ የመሰረዝ እድል ሊገጥመው እንደሚችል ይጠቁማሉ። ምክንያቱ ደግሞ በመቶ ሺዎች የሚቆሩ ሰዎችን እየገደለ ያለው ወረርሽኝ ክትባት አሊያም መድሃኒት የሚያገኝለት የሕክምናው ዓለም ጠበብት እስካሁን ባለመኖሩ ነው። ይህም ለረጅም ጊዜ የተዘጋጁ አትሌቶችን ልፋት ገደል መክተቱ ሳይበቃ ተስፋ ለመቁረጥና ልምምድ ለማቆም እንዳያስገድዳቸው አስጊ ሆኗል። በአትሌቲክስ ስፖርት ውጤታማ በሆነችው ኢትዮጵያ በርካታ አትሌቶች የዚህ ችግር ተጋላጭ ሊሆኑ እንደሚችል ይገመታል። ያም ሆኖ አትሌቶች ይህን ክፉ ጊዜ በብልሃት ማለፍ እንዳለባቸው ይታመናል። \nበቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን ለመወከል ተመርጠው የነበሩ አትሌቶች በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ያሉበት ሁኔታ ምን ይመስላል፣ መራዘሙ ምን አስከተለባቸው፣ አትሌቶችና አሰልጣኞችስ ይህ ወቅት እስኪያልፍ ምን እያከናወኑ ይቆያሉ በሚሉ ጉዳዮች ላይ አዲስ ዘመን የበሄራዊ ቡድኑን አባላት አነጋግሯል። \nየቶኪዮ ኦሊምፒክ ተሳታፊ የሆኑ አትሌቶችና አሰልጣኞች ተመርጠው ወደ ሆቴል እንዲገቡ በማድረግ ሂደት ላይ ሳለ የመራዘሙ ዜና መሰማቱን የሚገልጹት የብሄራዊ ቡድኑ አስተባባሪና የረጅም ርቀት ዋና አሰልጣኝ ሱፐር ኢንቴንደንት ሁሴን ሸቦ ናቸው። መንግስት ባወጣው አቅጣጫ መሰረትም\n የቡድኑ አባላት በየቤታቸው ተበትነው እንዲቆዩ ተወስኗል። ይሁን እንጂ አትሌቶች በያሉበት ቦታ ሆነው በሳምንት ለአምስት ቀናት በግላቸው ቀላል እንቅስቃሴዎችን እንዲሰሩ እየተደረገ ነው። ቀድሞ ከሚሰሩት ለሁለት ቀናት እያረፉ 80 በመቶ የሚሆንና አቋምን ጠብቆ ለማቆየት የሚሰሩ እንቅስቃሴዎች ላይ እንዲያተኩሩ አሰልጣኞች አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ይህንንም አሰልጣኞችና አትሌቶች ቴሌግራምን በመሰለ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እንዲሁም በስልክ እየተወያዩ ተግባራዊ እንደሚያደርጉም አሰልጣኙ ይጠቁማሉ። \nየረጅም ርቀት ሩጫዎች ከትንፋሽ ጋር የተያያዘ እንደመሆኑ ከስልጠናው ጎን ለጎን በተለየ መልኩ የሚታይ ነው። በመሆኑም አትሌቶች ከሌላው ህብረተሰብ በተለየ ከ2 እስከ 5 ሜትር የሚሆን መጠን ርቀታቸውን መጠበቅ እንዳለባቸው ይታመናል። ከዚህ ባሻገር የመተጣጠፍ፣ የጂምናስቲክና ሌሎች የማሳሳቢያ እንቅስቃሴዎችን በሚያከናውኑበት ወቅትም የተስተካከለ የአየር ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጥ እንዳለባቸው የሚጠቁሙት ዋና አሰልጣኙ ናቸው። ከአካል ብቃቱ ባሻገር በአእምሮም ብቁ እንዲሆኑና እንዳይረበሹም አሰልጣኞች ያስገነዝባሉ።\nየውድድሩ መራዘም በአትሌቶች ዘንድ ምን ተፅዕኖ እንዳሳደረ የብሄራዊ ቡድኑ አባልና ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ተሞክሮውን ያጋራል። ኦሊምፒክ በአራት ዓመት አንዴ የሚመጣ ውድድር\n እንደመሆኑ ለአትሌቶች ትልቅ እድል የሚፈጥርና በጉጉት የሚጠበቅ ነው። በመሆኑም አትሌቶች እድሉን በመልካም ለመጠቀም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ እንደነበሩም ያስታውሳል። እርሱም ከግል አሰልጣኙ ጋር በመሆን ከአንድ ዓመት በፊት እቅድ በማውጣት ልምምድ የጀመረ ሲሆን፤ በጃፓን ጥሩ ውጤት የማስመዝገብ እቅድ ነበረው። የኦሊምፒኩ መራዘም እስኪሰማ ድረስም በመልካም ዝግጅት ላይ ቆይቷል። \nብሄራዊ ቡድኑ ከተበተነ በኋላም በግሉ ከውድድር ውጪ የሚሰሩ እንቅስቃሴዎችን ከማድረግ ወደኋላ አለማለቱን በዶሃ የዓለም ቻምፒዮና የ5 ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊው አትሌት ሰለሞን ይጠቁማል። ስልጠናውም ቀድሞ ከሚሸፍነው ርቀት ያነሰ የትንፋሽ፣ ጂምናስቲክና ሌሎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን እንደሚያጠቃልል ይናገራል። ይህንንም ከታናሽ ወንድሙ ጋር በመሆን ርቀታቸውን በጠበቀ መልኩ በቤትና ወደ ጫካ በመሄድ ያከናውናሉ። ከአሰልጣኞችም አትሌቶች በብቃታቸው እንዲቆዩ ለማድረግ በስልክና በሌሎች መንገዶች ግንኙነታቸውን እንደቀጠሉ ያብራራል። \nየኦሊምፒኩ መራዘም በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ በአዘጋጇ ጃፓን፣ በተሳታፊ አገራት እንዲሁም አትሌቶች ዘንድ ተጽእኖ ማሳደሩ ይታወቃል። በአንጻሩ የጠቀማቸውም አልጠፉም፤ እነርሱም በጉዳት ምክንያት ለኦሊምፒኩ ብቁ\n ያልነበሩ አትሌቶችን መሆናቸውን አሰልጣኝ ሁሴን ይጠቁማሉ። ከዚህ ባሻገር ወጣትና ተተኪ አትሌቶችን ለአንድና ከዚያ በላይ ላለ ዓመት መራዘሙ የሚጠቅማቸውና ወደ ተወዳዳሪነት እንዲመጡ እድል የሚሰጥ እንደሚሆንም እምነት አላቸው። ምናልባትም ስጋት ሊሆን የሚችለው በጥሩ ብቃት ላይ ለሚገኙ ኤሊት አትሌቶች ሲሆን፤ ምክንያቱ ደግሞ በአንድ ዓመት ልዩነት ሊከሰት የሚችለውን የአቋም መውረድ ወይም ጉዳት ማስተናገድ ለመገመት አዳጋች በመሆኑ ነው። በጥቅሉ ሲታይም መዋዕለ ነዋይ ላፈሰሱ አገራትና በእቅድ ሲንቀሳቀሱ ለቆዩ አሰልጣኞችና ስፖርተኞች እንዲሁም ሌሎች አካላት ጉዳቱ በቀላሉ የሚገመት እንዳልሆነ ያስቀምጣሉ። በመሆኑም ይህ ለዓለም ስፖርት ከፍተኛ ኪሳራ የሚያስከትል መሆኑን ይናገራሉ። \nበኦሊምፒክ ለትልቅ ውጤት ከሚጠበቁት አትሌቶች መካከል አንዱ የሆነው ሰለሞንና ሌሎች የቡድን አጋሮቹ በጥሩ አቋም ላይ እያሉ ውድድሩ በመራዘሙ ደስተኛ እንዳልሆነ ወጣቱ አትሌት ይናገራል። ምክንያቱ ደግሞ አሁን ያለበትን ብቃት በቀጣዩ ዓመት ላያገኘው ስለሚችል ነው። ነገር ግን ቀዳሚው የሰው ልጅ ህይወት በመሆኑ ደስተኛም ባይሆን ከሁኔታዎች ጋር ራሱን ለማስማማት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ሌሎች አትሌቶችም ከክለብ የተበተኑ በመሆኑ በተለያዩ ስፍራዎች ይገኛሉ። በዚህ ምክንያትም ልምምድ ከማቋረጥ ይልቅ ከአቋማቸው እንዳይወርዱ ጥንቃቄ እያደረጉ ባሉበት ሆነው ዝግጅታቸውን ቢቀጥሉ መልካም እንደሆነ ምክረሃሳቡን ያጋራል። በክፍለ አገር የሚገኙ ባልደረቦቹም የሚያገኙትን መረጃ ለሌሎችም እንዲያጋሩ መክሯል። \nአሰልጣኙ በበኩላቸው ለአትሌቶች ‹‹ከህይወት በላይ ምንም የለም፤ የትኛውም ነገር ይደረስበታል። በመሆኑም መንግስትና የጤና ሚኒስትር የሚያወጧቸውን መመሪያዎችና አቅጣጫዎች መከተል አስፈላጊ መሆኑን ያስታውሳሉ። እጅን መታጠብ፣ ርቀትን መጠበቅ፣ በሰዎች መካከል ሲገኙ አፍና አፍንጫን መሸፈን እና የህመም ምልክቶች ሲሰሟቸው ለጤና ባለሙያዎች በፍጥነት ማሳወቅ አለባቸው›› ሲሉም ያስገነዝባሉ። ከአትሌቶች ወጪ ያሉ ዜጎችም ይህ ወቅት እስኪያልፍ ግንኙነታቸውን ከቀድሞው እንዲቀንሱና በመንግስት የተቀመጠውን አቅጣጫ ያለመወላወል ተግባራዊ እንዲያደርጉም ጥሪያቸውን ያቀርባሉ።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 26/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "27dde6a31e62972ae266112506eedf87" }, { "passage": "በዘንድሮው ክረምት ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ የዓለም ፈተና በሆነው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት የተነሳ ለ2021 እንዲራዘም መወሰኑ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ውስብስብ ፈተናዎች እንደሚገጥሙት የተለያዩ መላምቶችና ትንትኔዎች ከየአቅጣጫው መውጣት ከጀመሩ ሰንብተዋል። ኦሎምፒኩን በቀጣይ ዓመት ለማካሄድ ከተለያዩ ስፖርቶች የማጣሪያ ውድድሮች ጋር በተያያዘ ቁልፍ ጥያቄዎች እየተነሱ ሲሆን ከሌሎች ዓለም አቀፍ ውድድሮች ጋር እንዳይጋጭና የውድድር ቦታዎችን ከማቀናጀት አኳያ ውስብስብ ፈተናዎች ሊገጥሙት እንደሚችሉ ስጋቶች መኖራቸው አልቀረም። የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ቶማስ ባኽ እንደገለፁትም፣ የኦሎምፒኩን መራዘም ተከትሎ በርካታ ጥያቄዎች እየጎረፉ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ በቀጣይ ዓመት ኦሎምፒኩ የሚካሄድበት ወቅት እስኪወሰን ድረስ መጠበቅ የግድ ይሆናል። በኦሎምፒኩ የሚሳተፉ ሰላሳ ሦስት ዓለም አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖች አብዛኞቹ ኦሎምፒኩ ከሰኔ እስከ ሐምሌ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ቢካሄድ ምርጫቸው ነው። የተወሰኑት ፌዴሬሽኖች ደግሞ ከሚያዝያ እስከ ግንቦት እንዲካሄድ ፍላጎት አላቸው። ቶኪዮ የምታስተናግደው ኦሎምፒክ\nየበጋ እንደመሆኑ ከሐምሌ\nወር በፊት ቢካሄድ\nየሌሎች ዓለም አቀፍ\nውድድሮችን መርሃግብር መከለስ\nአንደኛው የቤት ስራ ይሆናል። በዚህ ዓመት ከቶኪዮ ኦሎምፒክ በፊት ሊካሄዱ የታሰቡ በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች መሰረዛቸውና መራዘማቸው ይታወቃል። እነዚህ የተሰረዙ ውድድሮች በቀጣይ ዓመት እንደሚካሄዱ ተስፋ የተደረገ ሲሆን የማይካሄዱ ከሆነ በብዙ መልኩ ኪሳራ እንደሚገጥማቸው ግልፅ ነው። ስለዚህ የራሳቸውን ኪሳራ የሚያሰሉ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች ለኦሎምፒኩ ቅድሚያ የሚሰጡበት እድል ጠባብ መሆን አንዱና ዋነኛው ፈተና እንደሚሆን ስጋት አለ። ኦሎምፒኩ በሚያዝያና ግንቦት የሚካሄድ ከሆነ በቶኪዮ ስጋት ከሆነው ከፍተኛ ሙቀት የሚገላገሉ ስፖርቶች የመኖራቸውን ያህል ፈተና የሚገጥማቸው ሊኖሩ እንደሚችሉ ይጠበቃል። ከሐምሌ መጨረሻ ጀምሮ ሊካሄድ ታስቦ በነበረው የቶኪዮ ኦሎምፒክ ከመሰረዙ አስቀድሞ በዚህ ወቅት ከፍተኛ ሙቀት በመኖሩ የማራቶንና የርምጃ ውድድሮች ወደ ሳፖሮ ከተማ መዛወራቸው ይታወቃል። በቀጣይ ዓመት ሚያዝያና ግንቦት ላይ የሚካሄድ ከሆነ ግን እነዚህ ስፖርቶች ወደ ቶኪዮ የመመለስ እድል ይኖራቸዋል። ይሁን እንጂ ኦሎምፒኩን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ለማስተላለፍ የተዋዋለው የአሜሪካን ኩባንያ በዚያ ወቅት ከምንም በላይ የሚጠብቀው የኤንቢኤና ሌሎች ታላላቅ የአሜሪካን ቅርጫት ኳስ ውድድሮች ስለሚኖሩበት የፍላጎትና የጥቅም ግጭቶች ሊፈጠር ይችላል። ይህ ደግሞ አንዱን ወገን በቢሊየን ዶላሮች ኪሳራ ላይ ሊጥል ስለሚችል ከባድ ፈተና እንደሚሆን ይታመናል። በተመሳሳይ በዚህ ወቅት ከዚህ ዓመት የተላለፉ በርካቶቹ ዓለም አቀፍ ውድድሮች የሚካሄዱበት መሆኑ ሌላ ጣጣ ይዞ መምጣቱ አይቀሬ ነው። በሌላ በኩል እንደ አትሌቲክስ ያሉ ውድድሮች ላይ አትሌቶች የኦሊምፒክ ሚኒማ የሚሰበስቡበት ወቅት እንደመሆኑ የጊዜ መጣበብና ሌሎች መጨናነቆች ይፈጠራሉ የሚል ምክኒያታዊ ስጋት ያሳድራል። ከአትሌቲክስ ውጪ ያሉ ስፖርቶችም ቢሆኑ አትሌቶቻቸው የኦሎምፒክ መስፈርቶችን ማሟላት የግዴታቸው ስለሚሆን ተመሳሳይ እክል ማስተናገዳቸው አይቀርም። ኦሎምፒኩ ከሰኔ እስከ ሐምሌ ቢካሄድ የሚለው ሃሳብ የተሻለ ቢመስልም በርካታ ውስብስብ ፈተናዎች እንደሚጠብቁት መጠቆም ይቻላል። በነዚህ ወራት ከሚካሄዱ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮች መካከል የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናና የዓለም ውሃ ዋና ቻምፒዮና ዋነኞቹቢሆኑም ውድድራቸውን ለመሰረዝ ፍቃደኛነታቸውን መግለፃቸው ይታወቃል። ይህ አበረታችና ለዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተስፋ የሰጠ ቢሆንም በነዚህ አካላት መካከል ተጨማሪ የውል ስምምነት እንደሚኖር ይጠበቃል። ይህ ምናልባትም ሌሎቹ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖችም ለኦሎምፒክ ቅድሚያ እንዲሰጡ ማነሳሳት ቢችልም ወቅቱ በጣም ከፍተኛ ሙቀት የሚኖርበት መሆኑ ለውድድሮች አስቸጋሪ እንደሚሆን ስጋት አሳድሯል። ለዚህም ከሰላሳ ዓመታት በፊት በቶኪዮና ኦሳካ ተካሂደው የነበሩት የዓለም አትሌቲክስ ቻፒዮናዎች ወቅት የነበረውን ሁኔታ ማስታወስ ተገቢ ይሆናል። ይሁን እንጂ ይህ ወቅት ከአሜሪካኖቹ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ውድድሮች ጋር አለመጋጨቱ እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ ሊቆጠር ይችላል። ምንም ይሁን ምንም\nኦሎምፒኩ በመራዘሙ ብቻ\nየጃፓን መንግስትን ጨምሮ\nበርካታ ባለድርሻ አካላት\nከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ\nውስጥ እንደሚገቡ ቀደም\nሲል ተዘግቧል። የጃፓኑ\nኦሎምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም\nገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ\nኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል\nተናግሯል። ዓለም አቀፉ\nኦሎምፒክ ኮሚቴ ለዚህ\nኪሳራ ስጋት ሰላሳ\nሦስቱንም ዓለም አቀፍ\nፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን\nየገባ ቢሆንም በቂ\nእንደማይሆን ታምኖበታል። ፕሬዝዳንቱ\nቶማስ ባኽም ኦሎምፒኩ\nመራዘሙን በገለፁበት ወቅት\nከባድ ኪሳራ እንደሚኖር\nበማመን ሁሉም ባለድርሻ\nአካላት መስዋዕትነት መክፈል\nእንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል።\nከባዱን መስዋዕትነት ማን\nእንደሚከፍልና ጫናው በየትኛው\nወገን ትከሻ ላይ\nሊወድቅ እንደሚችል ግን\nዛሬ ላይ ቆሞ\nበእርግጠኝነት መናገር አይቻልም።አዲስ ዘመን ሐምሌ 9/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "f104e25b8dd0f300cfdb5430c548ea40" } ]
d78d1eaed739df778b6cc838d9c2728d
b6305edd7b996674665952804200e176
አድዋን ለመዘከር በደብረ ብርሃን ከተማ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ይካሄዳል
በቀድሞዋ የስምንት መቶ ሜትር ኮከብ አትሌት ፋንቱ ሚጌሶ የተቋቋመው ‹ፋን ኢትዮጵያ የስፖርት አገልግሎት› ድርጅት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ ከተሞች የስምንት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮችን እያካሄደ ይገኛል።የተለያዩ ወቅታዊ ነገሮችን መነሻ በማድረግ የጎዳና ላይ ውድድሮችን በተለያዩ ከተሞች የሚያካሂደው ፋን ኢትዮጵያ ተተኪ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ለበርካታ አትሌቶች የውድድር እድሎችን እየፈጠረም ይገኛል።በተለይም የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች እምብዛም በማይካሄድባቸው ከተሞች ትኩረት በማድረግ አትሌቲክስን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ በመፍጠር በህብረተሰብ አቀፍ ስፖርት(ማስ ስፖርት) እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማድረግ ውጤቶች እያስመዘገበ ነው።በሀዲያ ሆሳዕና፣ አርባ ምንጭና ሀላባ ከተሞች በቅርቡ የተለያዩ የስምንት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድሮችን በስኬት በማድረግ በርካታ ህዝብ አሳትፎ ተወዳጅነትን ማግኘት ችሏል።በቀጣይም የካቲት 22 ቀን 2012 ዓ.ም የ124ኛው አድዋ ድል በዓል ዋዜማ በደብረ ብርሃን ከተማ ‹‹ኑ ለእምዬ ምኒልክ ክብር እንሩጥ›› በሚል መሪ ቃል ተመሳሳይ ውድድር ለማድረግ ዝግጅቱ እንደተጠናቀቀ ታውቋል።የፋን ኢትዮጵያ መስራች አትሌት ፋንቱና የደብረ ብርሃን ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ መርከብ ለማ ከትናት በስቲያ በውድድሩ ዙሪያ በኢልጌል ሆቴል መግለጫ ሰጥተዋል።በውድድሩ ከአርባ ሺ በላይ ህዝብ ለመሳተፍ የቲሸርት ኩፖን መግዛቱን የገለፀችው አትሌት ፋንቱ ታዋቂና ወጣት አትሌቶች በውድድሩ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ተናግራለች።በውድድሩ ውጤታማ የሚሆኑ ወጣት አትሌቶችን ከክለቦች ጋር ከማገናኘት ባለፈ ዓለም አቀፍ ውድድር እንዲያገኙ ሁኔታዎች እንደሚመቻቹም አትሌት ፋንቱ ጠቁማለች።ፋን ኢትዮጵያ ብዙም ባልተለመደው የስምንት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ደፍሮ በመግባት አበረታች ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ የገለጸችው አትሌት ፋንቱ ካለፉት ውድድሮች ልምድ በመቅሰም ወደፊት የሚያካሂዳቸውን ውድድሮች በተሻለ የጥራት ደረጃ ለማከናወን ጥረት እንደሚያደርግ አስረድታለች።መሰል ውድድሮች በየዞኑ እና ወረዳው ማካሄድ ቢቻል፤ ህዝቡ ስፖርቱንና አትሌቶችን በባለቤትነት ስሜት በመደገፍ የተለያዩ አካባቢዎችን የአትሌቶች መፍለቂያ ማድረግ እንደሚቻልም አትሌት ፋንቱ ጠቁማለች፡፡ፋን ኢትዮጵያ በተለያዩ ከተሞች የሚያደርጋቸው ውድድሮች ከስፖርታዊ ኩነትነቱ ባሻገር ሰላም፣ ፍቅርና አንድነትን የተመለከቱ መልዕክቶች የሚተላለፉበት ቢሆንም ውድድሩን ስፖንሰር በማድረግ በአጋርነት የሚሰሩ ድርጅቶች እንደሌሉ የተናገረችው አትሌት ፋንቱ መገናኛ ብዙሃንና የተለያዩ ከተሞች ውድድሩን ለማሳደግ ያሳዩትን ጥረት በመጥቀስ ምስጋና አቅርባለች።የደብረ ብርሃን ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ መርከብ በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ የምኒልክ የትውልድ ስፍራ የሆነችው ደብረ ብርሃንን ለማሳደግ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች መካሄዳቸው ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አብራርተዋል።ከተማ አስተዳደሩ የሰሜን ሸዋ ዞን መቀመጫ እንደመሆኑም የአድዋን ድል ለመዘከር ከሩጫ ውድድሩ ባሻገር የምኒልክን ጀግንነት የሚያሳዩ የተለያዩ መርሃግብሮችን ቀርፆ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ምክትል ከንቲባው ተናግረዋል።በውድድሩ ወቅት የጸጥታ ጉዳይ እንደማያሰጋ የገለፁም ሲሆን ዞኑና ከተማ አስተዳደሩ ከወዲሁ ዝግጅት ማድረጋቸውን አረጋግጠዋል።ፋን ኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች በማካሄድ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራት በሚደረገው አገር አቀፍ ርብርብ የራሱን ድርሻ እየተወጣ የሚገኝ ሲሆን፤ ዘንድሮ የሀላባን ዘመን መለወጫ ‹‹ሴራ›› በዓልን አስመልክቶ በሀላባ ከተማ ጥር 2 ቀን የተሳካ የስምንት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ለ3ኛ ጊዜ ማካሄዱ ይታወሳል።ከዚያ በፊትም በሆሳህና ከተማ ላይ የመጀመሪያ የጎዳና ላይ ውድድር ያካሄደ ሲሆን ለ2ኛ ጊዜ በአርባ ምንጭ ከተማ ማካሄዱ ይታወቃል።ውድድሮቹን  በየዓመቱ ለማካሄድ እንደታሰበም ታውቋል።አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 14/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27704
[ { "passage": "ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 20/2012 ዓ.ም (አብመድ) የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 22/2012 ዓ.ም በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የሚካሄደውን የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫን ያዘጋጀው ‹ወንፈል› የተሰኘ የተራድዖ ድርጅት ነው፡፡ ሩጫው የተዘጋጀበት ዓላማ ድርጅቱ በአማራ ክልል ጎንደርና ባሕር ዳር ለሚያስገነባቸው የሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህር ቤቶች ገቢ ለማሰባሰብ መሆኑን የድርጅቱ ገንዘብ ያዥ ዶክተር ይንገሥ ይግዛው በስልክ ተናግረዋል፡፡የጎዳና ላይ ሩጫው ከዋሽንግተን ዲሲ በተጨማሪ በሳን ሆዜ፣ በችካጎ፣ በአትላንታ፣ በሲያትል፣ በሎሳንጀለስ፣ በሳክራመንቶ እና በሌሎች ከተሞችም በተመሳሳይ ቀን የሚደረግ ይሆናል:: ወደፊትም በተለያዩ የአሜሪካ እና የአውሮፖ ከተሞች በማስፋት ገቢ የማሰባሰብ መርሀ ግብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ዶክተር ይንገሥ አስታውቀዋል፡፡ በተለያዩ ከተሞች በሚደረገው የጎና ላይ ሩጫም 100 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ይሰበሰባል ተብሎ ነው የሚጠበቀው፡፡በገቢ ማስገኛ መርሀ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሐፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ፣ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ሻለቃ ደራርቱ ቱሉ፣ የቀድሞው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው፣ ባለሀብቶች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶችም ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ነው ዶክተር ይንገሥ የተናገሩት፡፡ወንፈል በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ሕጋዊ ዕውቅና አግኝቶ እየተንቀሳቀሰ ያለ የተራድዖ ድርጅት ነው፡፡ ከተመሠረተ ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረው በጎ አድራጎት ድርጅቱ በባሕር ዳር እና በጎንደር የሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት በ2011 ዓ.ም ከክልሉ ትምህርት ቢሮ እና ከአልማ ጋር ስምምነት ተፈራርሞ ነበር፡፡ወንፈል በጎንደር እና በባሕር ዳር የሚያስገነባቸውን የሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለማጠናቀቅ 100 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ የአዳሪ ትምህርት ቤቶቹን ለማስጀመርም ከመጭው ቅዳሜ ጀምሮ መነሻ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር እንደሚያስጀምር ነው የተጠቆመው፡፡ዘጋቢ፡- ደጀኔ በቀለ", "passage_id": "df9bf7efa342f406b1cdcdb15b4ba6a0" }, { "passage": " አዲስ አበባ 123ኛውን የአድዋ ድል በዓል በስነ ጹሁፍ፣በእግር ጉዞ፣በፌስቲቫልና ግብር በማብላት በደማቅ  ሥነ ሥርዓቶች ልታከብር መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።ከተማ አስተዳደሩ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ ትናንት 123ኛው የአድዋ\nድል በዓል አከባበር ዙሪያ ከተባባሪ አዘጋጆች ጋር በመሆን ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል። የአድዋ የድል ጀግኖች አባቶቻችን ከወራሪዎች ጋር ባደረጉት ተጋድሎ የተገኘ  ድል መሆኑን የገለጹት ረዳት ፕሮፌሰሩ ይህን የሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች ታሪክ\nከትውልድ ትውልድ ለማስተላለፍ ዓላማ ባደረገ መልኩ የሚከበር መሆኑን ተናግረዋል።እንደ ረዳት ፕሮፌሰሩ ገለጻ የአድዋ ድል በዓል ለትውልድ ለማስተላለፍ በሚያስችል መልኩ በአዲስ\nአበባ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ለማክበር ዝግጅቱ ተጠናቋል። ዛሬ በብሄራዊ ቤተ-መዛግብት የፊልም ፌስቲቫል ይካሄዳል፤ ነገ ዓርብ  በዓሉን በተመለከተ የሥነ-ጥበብ ድግስ በጣይቱ ሆቴል ተዘጋጅቷል ብለዋል።\nበበዓሉ ዋዜማ  ምሽት  በጊዮርጊስ አደባባይ የተለያዩ ትዕይንቶችም ይካሄዳሉ። በዕለቱም በምኒልክ\nአደባባይና ሀውልት የአድዋ ሰማዕታትን የማስታወስ እና የማወደስ ሥነ-ሥርዓት ይካሄዳል። በመቀጠልም በዓሉ ከአጼ ምንልክ \nአደባባይ እስከ አድዋ ድልድይ  የእግር ጉዞ የሚካሄድ ሲሆን\nምሽት ላይም አርበኞችን እና የበዓሉ ታዳሚዎችን ግብር የማብላት ሥነ-ሥርዓትም የሚከናወን ይሆናል።በመጨረሻም የበዓሉ ዕለት  ከስምንት\nሰዓት ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ አዘጋጅነት የ “ክብር አድዋ ፌስቲቫል!” የሙዚቃ ድግስ በመስቀል አደባባይ ተዘጋጅቷል። የሙዚቃ\nድግሱ መግቢያ በነፃ ሲሆን በፌስቲቫሉ ላይ በርካታ የአገራችን የኪነ-ጥበብ ሰዎች የሚሳተፉ ይሆናል። ከተሳታፊዎቹ መካከል ድምጻዊ\nሙሀመድ አህመድ፣ቢቲጂ፣ኃይሌ ሩት ፣እሱባለሁ ይገኙበታል።አዲስ ዘመን የካቲት 21/2011", "passage_id": "d5ecff8df026cb7ead65ba1027fa59c6" }, { "passage": "ካኝነት የፊታችን እሁድ በመስቀል አደባባይ በሚካሄደው ሦስተኛው ከተማ አቀፍ የአካል ብቃት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እስከ 200ሺ ሰዎች እንደሚሳተፉ ተገለጸ፡፡ በስፖርታዊ መድረኩ የማርሻል አርት ፌስቲቫል እንደሚኖር ተጠቁሟል፡፡ የአዲስ አበባ\nስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ፋሲሊቲ ተሳትፎና ውድድር ዳይሬክተር አቶ ነጻነት ታከለ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት መረጃ፤ ሶስተኛውን የከተማ አቀፍ እንቅስቃሴ አስመልክቶ ቀድሞ ከነበሩት ሁለት የስፖርት ሁነቶች በተሻለ መልኩ ለማካሄድ ሰፊ ሥራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ህብረተሰቡ በመጀመሪያውና ሁለተኛው ዙር ተሳትፎ የስፖርታዊ እንቅስቃሴውን ዓላማ እየተረዳ በመሆኑ የተሳትፎ ቁጥሩም ቀድሞ ከነበረው ከፍ ይላል። ስፖርታዊ ሁነቱን ለየት ለማድረግም የማርሻል አርት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በየፌዴሬሽኖቹ አማካኝነት ይካሄዳል፡፡ በከተማዋ የሚገኙ 116 ወረዳዎችን የሚያሳትፈው ስፖርታዊ እንቅስቃሴው በወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ ስፖርት ቤቶች፣ 32 የስፖርት ፌዴሬሽኖች፣ የመንግስት ሰራተኞችና ከፍተኛ የስራ አመራሮች፣ ህጻናት አዋቂዎችና በአጠቃላይ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ መቅረቡን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ በዕለቱ ሁሉም የስፖርት አይነቶች እንደሚተገበሩና ለዚህ ስፖርታዊ ሁነቱን በበጎ ፈቃደኝነት በየስፖርት ዓይነቶቹ የሚመሩ አሰልጣኞች እንደሚያስተባብሩትም አስታውቀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ማብራሪያ፤ ስፖርታዊ እንቅስቃሴው የነዋሪዎችን ጤንነት ለማስጠበቅ፣ የተማሩ ስፖርተኞች ለመፍጠርና ማህበራዊ መስተጋብር እንዲጠናከር በሚል ዓላማ የተሰናዳ ነው፡፡ የዓላማው ተግባራዊነትም ወጣቱን በስፖርት ማነጽና ራሱን ከሌሎች ተጓዳኝ ሱሶች እንዲታቀብ በማድረግ መልካም ዜጋን ለማፍራት ያስችላል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴው በወር አንድ ጊዜ በከተማ ደረጃ የሚካሄድ ሲሆን፤ በአስተዳደር ተዋረድ ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ድረስ ባሉት መዋቅሮች በየሳምንቱ በቀናት ተወስኖ ተግባራዊ እንዲደረግ አቅጣጫዎች ተሰጥተዋል፡፡ ልምዱ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ በመሆኑ ከአዲስ አበባ ከተማ አልፎ በአገሪቷ የተለያዩ ከተሞችም ባህል ሆኖ ይቀጥላል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ የከተማዋን ህብረተሰብ ያሳተፈ የ‹‹ማስ\nስፖርት›› እንቅስቃሴ ለሁለት ጊዜ ያህል መካሄዱ ይታወሳል፡፡አዲስ ዘመን  ሐምሌ 26/2011 አዲሱ ገረመው", "passage_id": "6a5f2707523093e253e06836b20b45c5" }, { "passage": "በአምቦ ከተማ 16ኛው የባህል ስፖርቶች ውድድር እና 12ኛው የባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል «የባህል ስፖርት ተሳትፎአችን ለሰላምና ለአንድነታችን» በሚል መሪ ቃል በአምቦ ስታዲየም ዛሬ በይፋ ተጀመረ።የዕለቱ ፕሮግራም መከፈትን በይፋ ያበሰሩት ክብርት ዶክተር ሂሩት ካሳዉ የስፖርት ፋይዳዎች ዘርፈ ብዙ መሆናቸዉን በማስታወስ የብሔራዊ ስፖርት ፖሊሲያችን ባስቀመጠ አቅጣጫ መሠረት ህብረተሰቡን የበለጠ በባህል ስፖርቶች ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ በጥናት ላይ የተመሠሰተ ስትራቴጂዎችን ነድፎ ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በመናገር ዉድድሩና ፌስቲቫሉ በይፋ አስከፍተዋል።የአምቦ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተፈራ በዳዳ፣አና የኦሮሚያ ስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ናስር በበኩላቸው ፤አምቦ የሠላም እና የፍቅር ከተማ አንዲሁም ዉጤታማ አትሌቶችን እና ተዋቂ መዑራንን በማፍራት በመጥቀስ መልካም የቆይታ ግዜ ይሆን ዘንድ ምኞታቸውን ገልጸዋል።የኢትዮጵያ ባህል ስፓርቶች ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ሰለሞን አሰፋዉም በመቀጠል የዘንድሮዉ የባህል ስፓርቶች ፌስቲቫልና ዉድድር ዕድሜና ጾታ ሳይገድብ ህብረተሰቡን ባህል ስፖርቶች ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድድረግ በተለይ ስፖርቱ በሚፈጥርልን መልካም አጋጣሚ የአገራችን ሠላም በጋራ ለማክበርና ለማስከበር ነዉ ብለዋል።በአምቦ ከተማ በድምቀት እየተካሄደ በሚገኘው ውድድር በ13 የስፖርት አይነቶች የሚካሄድ ይሆናል ።የስፖርት አይነቶቹም ትግል፣ ገና ፣ ገበጣ፣ ፈረስ ጉግስ፣ ፈረስ ሸርጥ፣ ኮርቦ፣ ድብልቅ ኮርቦ፣ ሻህ፣ቡብ፣ ሁሩቤ ፣ ቀስት ፣ ድብልቅ ቀስት እና በባህላዊ ጨዋታዎች ይጠቀሳሉ:፡በውድድሩ አዲሰ አበባ ፣ድሬደዋ፣አማራ፣ደቡብ ብሔር ብሔረሰብ እና ህዝቦች፣ሐረሪ እና ኦሮሚያ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።በአምቦ ስታዲየም ድምቀቱን እንደጠበቀ ከካቲት 16 እስከ 24 ዓ.ም በአምቦ ከተማ የሚካሄድ ይሆናል።በዳንኤል ዘነበ\nፎቶ ሃዱሽ አብርሃ", "passage_id": "a5718585cdea3973a4b8034607dcf699" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳ የአፍሪካ\nመዲናዋ አዲስ አበባ\nበየዓመቱ ከምታካሂዳቸው ተናፋቂ\nትዕይንቶች መካከል በዓለም\nአቀፍ ደረጃ ዝና\nያተረፈው ታላቁ ሩጫ\nበኢትዮጵያ በቀዳሚነት ተጠቃሽ\nነው፡፡ ‹‹የሯጮች ሃገር››\nየሆነችው ኢትዮጵያ በሺዎች\nበሚቆጠሩ ሯጮች ጎርፍ\nየምትጥለቀለቅበት ይህ የ10\nኪሎ ሜትር መርሐ\nግብር፤ በአፍሪካ ቀዳሚው\nነው ፤ በዓለምም\nከምርጥ አስሮች ተርታ\nይመደባል፡፡ ‹‹ከሩጫም በላይ››\nየሚባልለት ታላቁ ሩጫ፤\nዘንድሮ በኮቪድ 19 ውስጥ\nየመጀመሪያውን ውድድር\nቀድሞ ከሚካሄድበት ህዳር\nወር ሁለት ወራትን\nበማዘግየት ትናንት አካሂዷል::\nበዓለም አቀፍ ደረጃ ለጎዳና ላይ ሩጫዎች ፈቃድ በሚሰጠው ተቋም (AIMS) እውቅና ያለው ይህ ውድድር 20ኛ ዓመቱን ዘንድሮ ሲያከብር 50ሺ ሯጮችን ለማሳተፍ እቅድ ነበረው፡፡ ነገር ግን በወረርሽኙ ስጋት ምክንያት ከቁጥሩ ከአንድ አራተኛ በላይ የሚሆነው ተቀንሶ 12ሺ 500 ሯጮችን አሳትፏል፡፡ ሩጫው የተካሄደው በሶስት\nተከፍሎ ሲሆን፤ የአረንጓዴ፣\nቢጫ እና ቀይ\nማዕበል   በሚልም\nመነሻውን በሶስት የተለያዩ\nአቅጣጫዎችና በ15 ደቂቃ\nልዩነት ያደረገ ነበር::በጎዳናው\nላይ በተደረገ ምልክት\nመሰረት ተሳታፊዎች ርቀታቸውን\nጠብቀው እንዲሳተፉ፣ ለጥንቃቄ\nሲባልም የአፍና አፍንጫ\nጭምብል እንዲያደርጉ፣ የሰውነት\nሙቀታቸውን እንዲለኩ እና\nሳኒታይዘር እንዲጠቀሙ ተደርጓል::ከዚህም\nጎን ለጎን ሩጫው\nበሚሸፍንባቸው መንገዶች የጤና\nባለሙያዎች በተጠንቀቅ ሲጠባበቁም\nተስተውሏል:: በመድረኩ ተገኝተው ሩጫውን ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ፤ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከስፖርታዊ ውድድርነቱ ባለፈ ለከተማዋ የቱሪስት መስህብ መሆኑን ጠቁመዋል::‹‹ይህ የሩጫ መርሐ ግብር ኢትዮጵያውያን በእድሜ፣ በጾታ እና በአካባቢ ሳንለያይ በአብሮነትና በፍቅር የምናካሂደው በመሆኑ ሁላችንም የከተማችን ውበትና ድምቀት የሆንበት ነው::ሆኖም በኮቪድ 19 ተግዳሮት ምክንያት በምንችለው ልክ ባለመሳተፋችን ቁጥሩ አነስተኛ ቢሆንም ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ምቹ አጋጣሚ ነው ብለዋል::አሸናፊነት ግን በሩጫ ብቻም ሳይሆን ሃገራችንን በማሳደግና ለውጥን በማስመዝገብ ድህነትና ጉስቁልናን በማሸነፍ ጭምር መመስከር ያለበት በመሆኑ ለዚህ ዓላማ ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን እንትጋ::እንደ ሩጫው ሁሉ ለሰዓት፣ ለደቂቃና ሰከንድ ዋጋ ሰጥተን ታላቅነታችንን እናረጋግጥ›› ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡በውድድሩ ላይ በሁለቱም ጾታ ከ100 ያላነሱ አትሌቶች ተሳትፈዋል ፤ ከኢትዮጵያውያኑ ባሻገር የኤርትራ፣ ኬንያ እና ኡጋንዳ አትሌቶችም ተካፋይ ሆነዋል::በዚህም በወንዶች የ2009 ዓ.ም አሸናፊው የአማራ ማረሚያው አትሌት አቤ ጋሻው ውድድሩን በበላይነት አጠናቋል::የደቡብ ፖሊሱ ታደሰ ወርቁ እና የሰበታው ሚልኬሳ መንገሻ ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ውድድራቸውን ፈጽመዋል::በሴቶች በኩልም የኢትዮ ኤሌክትሪኳ አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ፣ የንግድ ባንኳ አትሌት መድህን ገብረስላሴ እንዲሁም የመከላከያዋ አትሌት አባይነሽ አየለ ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ስፍራ በመያዝ የወርቅ፣ የብር እና የነሃስ ሜዳሊያዎች ተሸላሚ ሆነዋል::የ100ሺ ብር አሸናፊው አትሌት አቤ ጋሻው፤ ተወዳዳሪዎቹ ጠንካራ፣ ሩጫውም ከባድ ቢሆንም ጥሩ ውድድር ማካሄዱን ጠቁሟል::ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ዝግጅት ማድረግ ከባድ ቢሆንም በማህበራዊ ድረገጾች የሚሰጠውን ስልጠና ሲከታተል ቆይቷል::አትሌቶች ከውድድር ርቀው ከመቆየታቸው አኳያ ይህ ውድድር ወሳኝና አስፈላጊ ነው፤ ሌሎች ውድድሮችም በተመሳሳይ ቢዘጋጁ አትሌቶች ራሳቸውን እንዲመዝኑ፣ እንዲነቃቁና ስነ-ልቦናቸውንም ለመመለስ የሚረዳቸው መሆኑንም አመልክቷል::ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ተጠባባቂ የሆነው አትሌቱ ጥሩ ዝግጅት በማድረግ ሃገሩን የመወከል አላማ እንዳለውም ተናግሯል::በሴቶች የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቀችው ጽጌ ገብረሰላማ በበኩሏ፤ ከፍተኛ ፉክክር በተካሄደበት ውድድር አሸናፊ በመሆኗ ደስተኛነቷን ትገልጻለች:: ከጉዳት መልስ ዳገት በበዛው በዚህ ውድድር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችው አትሌቷ ፤ ለቶኪዮ ኦሊምፒክ በ5ሺ ሜትር ተመራጭ በመሆኗ ዝግጅቷን አጠናክራ ውጤት ለማስመዝገብ የምትጥር መሆኗን ጠቁማለች::በውድድሩ አሸናፊ የሆኑት አትሌቶች የ100ሺ፣ 30ሺ እና 12ሺ ብር ሲበረከትላቸው፤ እንደየደረጃቸው ሜዳሊያ እና ዋንጫም ወስደዋል::ከአትሌቶች ባለፈ የአካል ጉዳተኞች፣ አምባሳደሮች፣ የባዶ እግር እንዲሁም የበጎ ፈቃድ ሯጮች ዘርፍም በቀዳሚነት ሩጫውን ላጠናቀቁ ሽልማት ተሰጥቷቸዋል::ሽልማቱን ለአሸናፊዎች የሰጡትም በክብር እንግድነት የተገኙት አንጋፋዎቹ ብርቅዬ አትሌቶች ብርሃኔ አደሬ፣ ጌጤ ዋሚ እና አሰለፈች መርጊያ ናቸው::ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን ከአትሌቶች ባሻገር ከምስረታው ጀምሮ ተሳትፎ ያላቸው ቋሚ ሯጮችም አሉት::ከእነዚህም መካከል አንዱ የፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ ነዋሪ የሆኑት አቶ ለማ ከበደ፤ ሩጫው በየጊዜው እያደገና ተሳታፊውም እየጨመረ መሄዱ ያለማቋረጥ እንዲሳተፉ ያደረጋቸው መሆኑን ይገልጻሉ::ከራሳቸው አልፈው ቤተሰብና ጓደኞቻቸውንም በመጋበዝ የተሳታፊ ቁጥሩን በማሳደግ በኩልም ሚና ነበራቸው::ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከሃገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታወቀ የመጣ እንደመሆኑ ወደፊት ከዚህም በላይ ሊያድግ የሚችል ተወዳጅ ሩጫ እንደሚሆም ተስፋ አላቸው::ለዚህ ውድድር ሲሉ ከሚሰሩበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጡት አቶ ዮሴፍ አሰፋ በበኩላቸው፤ ሩጫው ከስፖርት ውድድርነቱ ባሻገር የአንድነትና የወንድማማችነት ተምሳሌት መሆኑን ይጠቁማሉ::ከተለያዩ አካባቢዎች የሚሳተፉ ሯጮች በአንድ ላይ መሮጣቸው አንድነትን የሚያጠናክርና መተባበርን የሚጨምር እንደሆነም ያረጋግጣሉ::በአትሌቲክስ ትልቅ እውቅና ላላት ኢትዮጵያ መሰል ውድድር ለስፖርቱ ትልቅ ፋይዳ ስላለው አትሌቶች በርትተው እንዳለፈው ጊዜ ሃገራቸውን በስኬት ለማስጠራት ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል:: የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጠንሳሽ ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ በበኩሉ፤ ከተሳታፊዎች ቁጥር ማነስ ባሻገር ሩጫው ጥሩ እንደነበረ ነው የገለጸው::የሩጫው መነሻና መድረሻ የተለያዩ ቦታዎች መሆኑ ለአዘጋጆች ከባድ ቢሆንም፤ የሩጫ ፈቃዱ ሲሰጥ የተቀመጡ የጥንቃቄ መስፈርቶችን በማሟላትና በተሻለ ቅንጅት መጠናቀቁን አስታውቋል::የቱሪስት መስህብ በሆነው በዚህ ሩጫ ከዚህ ቀደም በርካታ የውጪ ሃገራት ዜጎች እንደሚሳተፉ ቢታወቅም ከወረርሽኙ ስጋትና ከጉዞው ጋር በተያያዘ በብዛት ተሳታፊ ሳይሆኑ ቀርተዋል::ሆኖም ኢትዮጵያ በጥንቃቄ፣ በሰላምና በትብብር ይህን መሰል ትልቅ ስፖርታዊ ውድድርን የማስተናገድ አቅም ያላት መሆኑን ያስመሰከረችበት ነው ብሏል ::በርካታ የውጪ ሃገራት የመገናኛ ብዙሃን ለውድድሩ ሽፋን መስጠታቸውም ኢትዮጵያ እንደምትችል እና በጸጥታም በኩል ያለውን ሁኔታ የሚያሳይ እንዲሁም መልካም ገጽታዋን የሚያጎላም እንደሆነ ተናግሯል ::ስፖርት ሰዎችን መሳቢያ መሳሪያ መሆኑን የሚጠቅሰው ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ‹‹ስፖርት አለ ማለት፤ ሰላም፣ እድገት፣ ጤንነት እንዲሁም እንቅስቃሴ አለ ማለት ነው›› ብሏል ::ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከዚህም በዘለለ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ለሃገራቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ድልን ያስመዘገቡ አትሌቶችን ሲያፈራ እና ህብረተሰቡንም ወደ ስፖርት እንዲገባ ንቅናቄ የፈጠረ እንደሆነም አመልክቷል ፡፡ የዘንድሮው ውድድር የተሳታፊ ቁጥርና የስፖንሰሮች ድጋፍ በመቀነሱ፣ ለጥንቃቄ ሲባል በወጣው ወጪ፣ የውድድር ተሳታፊ አትሌቶች የኮቪድ 19 ምርመራ ለማድረግ እንዲሁም የውድድሩ ማስጀመሪያ እና መጨረሻው በተለያየ ቦታ መካሄዱ ሁለት ቦታዎች ላይ መድረክ ማዘጋጀት ከባድ እንደነበረና ከዚህ ቀደም የነበረው አንጡራ ሃብት በዚህ ውድድር መውጣቱንም ጠቁሟል::ይሁንና ሩጫው በስኬት በመጠናቀቁ የአዲስ አበባ ነዋሪ፣ ከተማ አስተዳደሩ፣ የጤና ጥበቃ እንዲሁም የከተማዋ ጸጥታ አስከባሪ አካላት ምስጋና እንደሚገባቸውም ገልጿል::", "passage_id": "b39fda700c2c70467ce1020a281120b8" } ]
d53f7e0957be92198763882ceebbea66
1025b616479452c4ebf4f8a54e79c921
ሳይበራ የጠፋው የረጅም ርቀት ኮከብ
 በስፖርቱ ዓለም በወጣትነት እድሜ ላይ የሚገኙ ጀግኖች በድንገተኛ አደጋ ሕይወታቸው የሚያልፍበት አጋጣሚ የተለመደ ነው። ይሁን እንጂ በአጭርም ይሁን በረጅም ጊዜ ሕመም ሕይወታቸው የማለፉ ዜና ሲሰማ የብዙዎችን ልብ የሚሰብርና ያልተለመደ መሆኑ አይቀርም። ከሳምንት በፊት አሜሪካዊው የቅርጫት ኳስ ኮከብ ኮቤ ብርያንት በገዛ ሄሊኮፕተሩ በደረሰበት የመከስከስ አደጋ በአርባ ዓመቱ ከታዳጊ ልጁ ጋር ሕይወቱ በማለፉ ዓለማችን አዝናለች። ከዚህ የሃዘን ድባብ ሳትወጣም ከቀናት በፊት ኢትዮጵያዊው የረጅም ርቀት አትሌት አባዲ ሃዲስ በህመም ምክንያት በመቖለ ሃይደር ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ጥር 26/2012 ዓ.ም. ምሽት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ ሳምንቱ ለስፖርት ቤተሰቡ መጥፎ ሆኖ አልፏል። በተለይም ኦሊምፒክን ጨምሮ በዓለም አቀፍና አህጉራዊ ውድድሮች አገሩን በመወከል የሚታወቀው የ22 ዓመት ወጣት አትሌት አባዲ ሀዲስ ሕልፈተ ሕይወት ለኢትዮጵያውያን አስደንጋጭና መሪር ሃዘን ነው። አትሌት አባዲ ሃዲስ ባደረጋቸው ውድድሮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አደባባይ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ በማድረግ በአትሌቲክሱ ውጤታማ ከሆኑት አትሌቶች ተጠቃሽ ከመሆኑ ባሻገር እድሜው ገና ብዙ መስራት የሚችልበት ወጣት መሆኑ ሃዘኑን መሪር ያደርገዋል። አትሌት አባዲ ሃዲስ በትግራይ ክልል ማይጨው ከተማ ልዩ ስሙ እንዳመሆኒ ወረዳ ጥር 27/1990 ዓ.ም የተወለደ ሲሆን የአትሌቲክስ ህይወቱን በእንዳመሆኒ የአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ጣቢያ ነበር የጀመረው። በመቀጠልም በማይጨው አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ገብቶ መደበኛ ስልጠናውን ሲያጠናቅቅ ትራንስ ኢትዮጵያ አትሌቲክስ ክለብ በመቀላቀል ህይወቱ እስካለፈበት እለት ድረስ በውጤታማነት ክለቡን፣ ክልሉንና አገሩ ሲያስጠራ የነበረ ጀግና ነው። አትሌት አባዲ በብራዚል ሪዮ ዴ ጄኔሮ በተካሄደው የ2016 የኦሊምፒክ ጨዋታዎች በ10 ሺ ሜትር 27፡36.34 በሆነ ሰዓት 15ኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀ ሲሆን በቅርቡ በዶሃ ኳታር በተካሄደው የ2019 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ5ሺ ሜትር አገሩን ወክሎ ተሳትፏል። በለንደን በተካሄደው የ2017 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናም በ10ሺ ሜትር 26፡59.19 በሆነ ሰዓት 7ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል።በኡጋንዳ ካምላ በ2017 በተካሄደው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና በአዋቂ ወንዶች 10 ኪሎ ሜትር. ውድድር በ28፡43 ሰዓት 3ኛ ደረጃ በመያዝ የነሐስ ሜዳልያ ለአገሩ ማስመዝገብ የቻለው አትሌት አባዲ በሞሮኮ ራባት በ2019 በተካሄደው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በ10ሺ ሜትር 28፡27.38 7ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቅ ችሎ ነበር። በ2016 በተካሄደው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ10ሺ ሜትር 28፡43.2 በሆነ ሰዓት 1ኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀበት አጋጣሚም ከስኬቶቹ መካከል ይጠቀሳል። አባዲ ሩጫን በዓለም አቀፍ ደረጃ በ 5ሺ ሜትር ጀምሮ በ 5ሺ ሜትር ከአራት ወር በፊት በዶሃ የዓለም ቻምፒዮና ላይ አገሩን ወክሎ በመሳተፍ ይቺን ምድር ተሰናብቷል። አባዲ በአትሌቲክስ ሕይወቱ አገሩን ወክሎ በተሳተፈባቸው ውድድሮች ከግል ውጤቱ ይልቅ ለአገር ቅድሚያ የሚሰጥ፣ የቡድን ስራ ጠፍቷል በሚባልበት ወቅት ለቡድን ውጤት የሚጨነቅ ሩቅ አሳቢ ኮከብ መሆኑን በቅርብ የሚያውቁት ምስክርነታቸውን የሰጡት ሕይወቱ ከማለፉ በኋላ አይደለም። ታታሪው ወጣት አትሌት በአትሌቲክስ ሕይወቱ አንድ አትሌት ሊደርስበት የሚመኘው ደረጃ ላይ በአጭር ጊዜ መድረስ ቢችልም ህልሙና ግቡ እንዲህ በአጭሩ የሚቋጭ አልነበረም። አባዲ ሕይወቱ ከማለፉ አስቀድሞ በረጅም ርቀት ዓለማችን ላይ ካሉ ኮከብ አትሌቶች አንዱ ቢሆንም የበለጠው ስኬት ከፊት የሚጠብቀው እንደነበር ብዙዎች በቁጭት ይናገራሉ። ይህ የረጅም ርቀት ኮከብ እንዳለው አቅምና ህልም እስካሁን አላበራም። በረጅም ርቀት በበለጠ ስኬት የሚያበራበት ጊዜ ከፊቱ ቢጠብቀውም ሳይበራ ሞት ቀድሞታል። ከሩጫ ችሎታው በተጨማሪ በባህሪው ዝምተኛና ሰው ቀና ብሎ የማያይ የመልካም ፀባይ ባለቤት የሆነው አባዲ በአጭር ጊዜ የደረሰበት የስኬት ጫፍ ግን በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ታሪክ ውስጥ ሲታወስ እንዲኖር ያደርገዋል። አባዲ በዓለም አቀፍ ደረጃ 34 ውድድሮችን አድርጓል። የ 1 ሜትር ከ70 ሳንቲ ሜትር ቁመት እንዲሁም 63 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ኮከብ ዓለም አቀፍ ውድድር ማድረግ የጀመረው እ.ኤ.አ 2015 በ5 ሺ ሜትር ሲሆን በወቅቱ 13:13፡17 በመሮጥ 13ኛ ደረጃን አገኘ። የመጨረሻውን ውድድርም በዶሀ ዓለም ቻምፒዮና በ 5 ሺ ሜትር 13:42፡89 መሮጥ ችሏል። በ 3 ሺ ሜትር 7:39፡10 እ.ኤ.አ በ2018 ካናዳ ላይ ያስመዘገበው ፈጣን ሰዓቱ ሲሆን በተመሳሳይ ዓመት በ 5 ሺ ሜትር 12:56፡27 ብራሰልስ ላይ ያስመዘገበው የርቀቱ የግሉ ፈጣን ሰዓት ነው። በ10 ሺ ሜትር 26:56፡46 በሄንግሎ ያስመዘገበው ፈጣን ሰዓት ሲሆን በግማሽ ማራቶን 58:44 ቫሌንሲያ ላይ ያስመዘገበው ሰዓት ወደ ፊት ብዙ ተስፋ እንዲጣልበት ያደረገ ነው። አባዲ በአራት ዓመት የሩጫ ህይወት ቆይታው 3 ሺ ሜትርን ሁለት ጊዜ ሮጧል። ስኬታማ በሆነበት 5 ሺ ሜትር ደግሞ አስራ ሦስት ውድድሮችን አድርጓል።አገሩን በኦሊምፒክና በዓለም ቻምፒዮና በወከለበት የ10 ሺ ሜትር ርቀት ዘጠኝ ውድድሮችን ሲያደርግ በ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር አንድ ጊዜ ብቻ ሮጧል። 21 ኪሎ ሜትር ወይም ግማሽ ማራቶንን አራት ጊዜ በመወዳደር ትልቅ ተስፋ የሰጠ ሰዓት ማስመዝገቡም ይታወቃል። በአገር አቋራጭ ውድድሮች በ9፣ 10.4፣10.796 እና 11.1 ኪሎ ሜትር ውድድሮች አንዳንድ ጊዜ ብቻ ሮጧል። አዲስ ዘመን የካቲት 1 / 2012 ዓ.ም ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=26976
[ { "passage": "አፍሪካ በ 2017/18 የውድድር ዓመት በዓለም አቀፍ ይሁን በአህጉራዊ የስፖርት መድረክና ሁነቶች ስትታወስ ስኬትም ውድቀትንም አስተና ግዳለች። አሳዛኝ ታሪኮችንም አሳልፋለች። ከእነዚህ የውድድር ዓመቱ አብይት ሁነቶች መካከል ደግሞ የሚከተሉት ከሁሉ ልቀው ይታወሳሉ።አሳፋሪው የአፍሪካ የዓለም ዋንጫ የተሳትፎ ታሪክ\nአፍሪካውያኑ ኮከቦች ምንም እንኳን በተለያዩ ታላላቅ ሊጎች አገራቸውንና ስማቸው ከፍ አድርገው ማስጠራት ቢችሉም በአህጉር አቀፍ ውድድሮች በተለይ በታላቁ የዓለም ዋንጫ የሚያሳዩት አቋም ግን ብዙዎችን ግር ያሰኘ ነበር።በእርግጥ አፍሪካውያኑ ተጫዋች በዓለም ዋንጫው መድረክ መገኘት የሚያጎናፅፈውን ክብርና የሚሰጠውን የተለየ ስሜት ጠንቅቀው ቢያውቁትም ከተሳትፎ ባለፈ በመድረኩ ላይ አዲስ ታሪክ መስራት የምንጊዜም ህልምና ምኞታቸው ነው።ይሁንና ይህ መሻታቸው ዓለም ዋንጫው ከተጀመረ ዓመታትን ተሻግሮም ውጤት ማምጣትና በዋንጫ መታጀብ አልሆነለትም።ከወራት በፊት በተካሄደው 21ኛው የሩሲያ የዓለም ዋንጫ በሦስት የሰሜንና በሁለት የምዕራብ አፍሪካ አገራት የተወከለችው አፍሪካ፣ እግር ኳሳዊ የታሪኩ አሸናፊነት አቅጣጫን የመቀየር አቅም ያላቸው ተጫዋቾችን ይዛ ሞስኮ ብትደርስም የፈለገችውን ግን ማግኘት አልቻለችም።\nከዓለም ዋንጫ መጀመር አስቀድሞ በርካቶች በዓለማችን ታላላቅ ሊጎች ትልቅ ተፅዕኖ መፍጠር የቻሉና አገራቸውን ወክለው ሩሲያ ያቀኑ ኮከቦችን ዋቢ በማድረግ በዘንድሮው ፍልሚያ አፍሪካ የተሻለ ውጤት እንደሚኖራት ቢተነብዩም በሞስኮ ሰማይ ስር የሆነው ግን ከዚህ ፈፅሞ የተቃርኖ ሆኗል። ከአህጉሪቱ የመድረክ ተወካዮች አንድም ብሄራዊ ቡድን ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ አልቻለም።በታሪክም እጅግ በደካማና አሳፋሪ አቋም ና ውጤት ወደመጡበት ተመልሰዋል።ከዚህ ቀደም ማለትም ከ1986 የሜክሲኮ የዓለም ዋንጫ ወዲህ አህጉሪቱን ከወከሉ ብሄራዊ ቡድኖች ቢያንስ አንድ ቡድን ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ችሏል።ይህ ውጤታቸው ደግሞ እ.ኤ.አ 1998 የፈረንሳዩ የዓለም ዋንጫ የተሳታፊ አገራት ቁጥር ወደ 32 ፤የአፍሪካ ተወካዮች ደግሞ አምስት ሳይሆን ሦስት አገራት ብቻ ሆነውም ያልተቋረጠ ነበር።ከዚህ በተቃርኖ አፍሪካውያኑ በየሩሲያው መድረክ ያሳዩት የወረደ እግር ኳሳዊ ብቃት ከስፔኑ የዓለም ዋንጫ ማለትም ከሰላሳ ስድስት ዓመታት በኋላ ታይቶ የማይታወቅ አድርጎታል። በሩሲያ ምድር ከአሥራ አምስት ጨዋታ አፍሪካውያኑ ውጤት ማምጣት የቻሉት በሦስቱ ብቻ ነው።በአሥሩ ጨዋታዎች ተሸንፈዋል። ግብፅ፤ሞሮኮ፤ ቱኒዚያና ናይጄሪያ የተሰናበቱትም ገና ከምድባቸው ነበር። በተለይ በመድረኩ የተሻሉ ኮከቦችን የያዙት አገራት አንድም የረባ ጨዋታና ውጤት ሳይዙ መመለሳቸው ብዙዎችን አነጋግሯል።የኪፕቾጌ አዲስ ታሪክ\nአፍሪካ በዓመቱ ከእግር ኳስም በላይ በአትሌቲክሱ ስሟን ከፍ አድርጋ ታይታበታለች። በተለይ የኬንያው አትሌት ኢሊዩድ ኪፕቾጊ ስም ከሁሉ ገኖ ተሰምቷል። አትሌቱም በዓመቱ በማራቶን የውድድር የምንጊዜም ፈጣን ሰዓት አስመዝግቧል። አትሌቱ በጀርመን በርሊን በተካሄደው የማራቶን ውድድር 2፡1፡39 ሰከንድ በመግባት የዓለም ክብረ ወሰን ሰብሯል።የ 33 ዓመቱ አትሌት በአውሮፓውያኑ 2014 በአገሩ ልጅ ደኒስ ኪሜቶ ተይዞ የነበረውን ሰዓት በ1፡20 ሰከንድ አሻሽሎ በአስደናቂ የአሯሯጥ ብቃት የርቀቱን ክብረ ወሰን በባለቤትነት ተቆጣጥሯል። ከወራት ቀድሞም በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ማህበር የዓመቱ ምርጥ ወንድ አትሌት አሸናፊ በመሆን ልፋቱን የሚመሰክር ክብርን ተቀናጅቷል።\nየሞሃመድ ሳላህ ከፍታ\nዓመቱ አፍሪካ በድንቅ እግር ኳሳዊ ጥበብ የተካኑ ተጫዋቾች እንዳሏት ግብፃዊው የሊቨርፑሎች ኮከብ መሃመድ ሳላህ ለዓለም ያስተዋወቀበትም ነበር ።በእግር ኳሳዊ የጥበብ ልህቀቱ ዓለምን ያስደመመው ሞሃመድ ሳላህ፤ከሮማ በ 34 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ሊቨርፑል ከተዘዋወረ በኋላ በውድድር ዓመቱ በ 37 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች 31 ግብ ማስቆጠር ችሏል፡፡ሉዊስ ሱዋሬዝ 2013/14፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ 2007/08 እንዲሁም አለን ሺረር 1979 እስከ 1996 በአንድ ውድድር ዓመት ካስቆጠሯቸው 38 ጎሎች ጋር እኩል በማስቆጠር ክብረወሰኑን ተጋርቷል።በአስደማሚ ብቃቱ የሚማረኩ ወዳጆቹ ግብፃዊው ሜሲ ሲሉ የሚያሞካሹት ሳላህ፤ በተወዳጁ ሊግ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋችም ተብሎም ተመርጧል።በፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ተጫዋቾችና ጸሐፊዎች ማህበር የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች በመባል ሽልማት አግኝቷል። በዓመቱ በሁሉም ጨዋታዎች 44 ግቦችን ለሊቨርፑል ማስቆጠር ችሏል፡፡ፈርኦኖቹን ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ሩሲያው ዓለም ዋንጫ እንዲያልፉ በማድረግ የቁርጥ ቀን ልጃቸው መሆኑን አስመስክሯል። በውድድር ዓመቱ ካስቆጠራቸው ግቦች በላይም ይህች ግብ ክብርና ሞገስን አጎናፅፋዋለች።ምትሃተኛው ግራ እግር ተጫዋች በውድድር ዓመቱ ባሳያው ምርጥ ብቃት በአህጉር ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ልቆ ታይቷል።የፊፋ የአውሮፓ ዓመቱ ምርጥ ተጫዋቾች እጮዎች ውስጥም ስሙን አካቷል። ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የቢቢሲ የዓመቱ የአፍሪካ ኮከብ እግር ኳስ ተጫዋች በመሆን ተመርጧል። በዚህ ታሪኩም ከናይጄሪያዊው ኮከብ ከአውስቲን ጄይ ጄይ ኦኮቻ ጋር ተስተካክሏል። ሳላህ በውድድር ዓመቱ ባሳየው ድንቅ ብቃት የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋችነት ክብርም ተሰጥቶታል። ዓመቱም የተጫዋቹን ብቃት በማስመስከር ስሙን ከፍ አድርጎ ያስጠራባት ሆኗል።የፊፋና የአፍሪካ አገራት ፍጥጫ\nዓመቱ በተለይ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ፊፋ ከአፍሪካ አገራት ጋር እስጣ ገባውን አጧጡፎ የታየበት ሆኖም አልፏል። በተለይ ጋና፤ ናይጄሪያ ሴራሊዮን የመሳሰሉ አገራት የፊፋን ህግ በተላለፈ ሁኔታ ፖለቲካና እግር ኳስን ቀላቅለው መታየታቸውን ተከትሎ የተቋሙን ቁጣና ቅጣት አስተናግደዋል።ጋና እና ናይጄሪያ ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳደር ጋር ለገቡበት እስጣ ገባ በቶሎ ለመቋጨት በአገራቱ እግር ኳስ ውስጥ የተንሰራፋውን የአመራር ሽኩቻና ገሃድ የወጣ የሙስና ቅሌት ለማስወገድ መፍትሄ የሚሉትን እልባት ሰጥተዋል።ሴራሊዮን በአንፃሩ እንደ ናይጀሪያና ጋና የቤት ሥራዋን በሚገባ መወጣት ባለመቻሏ የፊፋን እገዳ ማስተናግድ ግድ ብሏታል።የአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ የሚስተዋለው ሙስና ከጊዜ ወደ ጊዜ ጥርሱን ማግጠጡ የታየውም በዚሁ ዓመት ነው።ተግባሩም የአህጉሪቱን እግር ኳስ በበላይነት ከሚመራው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አመራሮች ጨምሮ እስከ ብሄራዊ ፌዴሬሽን አመራሮች፤ አሰልጣኞች ዳኞችና ተጫዋቾች ዘለቆ ታይቷል።አዲሱ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ካፍ ፕሬዚዳንት አህመድ አህመድ ወደ ስልጣን እንደመጡ ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ የበላይ አካል ፊፋም ጋር በመሆን የፀረ ሙስና ፍልሚያቸውን ጀምረዋል።የጋና እግር ኳስ ማህበር ፕሬዚዳንት ክዌሲ ንያንታኪ «ስልጣናቸውን በመጠቀም ያልተገባ ጥቅም ማግኘትና ሰዎችን በማታለል 65 ሺህ ዶላር ተቀብለዋል» የሚል ክስ በመክፈት ባደረገው ምርመራ በተለይ ቁጥር «12» በሚል ርዕስ በምርመራ ጋዜጠኛው አነስ አርሜይው አናስ የተሰራው በጋና እግር ኳስ ውስጥ ስላለው ሙስና የሚያሳይ ዘገባ ፕሬዚዳንቱ ጥፋተኛ ስለመሆናቸው አረጋግጧል።በመቅረፀ ምስል የተደገፈውን ማስረጃውን የተመለከተው የፊፋ የሥነ ምግባር ኮሚቴ ግለሰቡ በብሄራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከማንኛውም የእግር ኳስ እንቅስቃሴ ዕድሜ ልክ አግዷቸዋል። ከዚህ ቅጣት ባሻገር እ.ኤ.አ ከ 2017 ጀምሮ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ካፍ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትና የእንግሊዘኛ ቋንቋ ተናጋሪ የሆኑ የአፍሪካ አገሮችን በመወከል እ.ኤ.አ ከ2016 ጀምሮ የፊፋ ምክር ቤት አባል ሆነው የሰሩትን ግለሰብ አምስት መቶ ሺ ዶላር እንዲከፍሉ ውስኗል።የአፍሪካ እግር ኳስ ምልክቶች ስንብት\nዓመቱ የአፍሪካ እግር ኳስ ምልክቶች የነበሩ ተጫዋቾች ጫማ የሰቀሉበት ሆኖም አልፏል። የቼልሲውና የአይቮሪኮስት ምልክት ዲዲየር ድሮግባ ሁለት አሥርት ዓመታት የዘለቀውን የእግር ኳስ ህይወቱን በመቋጨት ጫማ የሰቀለው በዚህ ዓመት ነው።በ24 ሚሊዮን ፓውንድ ቸልሲን በ2004 የተቀላቀለው ድርጎባ ላለፉት 8 ዓመታት በስታንፎርድ ብሪጅ የተለያዩ ድሎችን አጣጥሟል።በሰማያዊው መለያ ለ381 ጊዜያት ተሰልፎ በመጫወት 164 ግቦችን ከመረብ በማዋሃድም ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ነው። ያስቆጠራቸው የግብ ብዛትም በቼልሲ አራተኛው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ያደርገዋል። ስታምፎርድ ብሪጅን እንደቤቱ የሚመለከተው ድሮግባ፤ አወዛጋቢው የሚል ቅጽል ያላቸው ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ «በአውሮፓ ምርጡ ተጫዋችና መልካም ስብዕና ያለው» ሲሉም ያንቆለጳጵሱታል።በሰማያዊዎቹ ቤት ቆይታውም፤አራት የፕሪምየር ሊግና የኤፍ ኤ ዋንጫዎችን አንስቷል።ሦስት የሊግ ካፕ፣ ሁለት ኮሚዩኒቲ ሺልድ እንዲሁም በ2012 የውድድር ዓመት አንድ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫም አሳክቷል።ኢኳቶሪያል ጊኒ እ.ኤ.አ 2015 ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ ጋናን በመርታት ዋንጫውን ለማንሳት ችሏል።የፈርኦኖቹ ግብ ጠባቂ አል ሃድሪ ከሩሲያው የዓለም ዋንጫ ማግስት በ45 ዓመቱ ራሱን ከእግር ኳስ ያገለለበት ዓመትም ነው። በ 22 ዓመታት ቆይታው በክለብም ሆነ በብሄራዊ ቡድን በድል የተንቆጠቆጡ ዓመታትን አሳልፏል።የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅ እጦት\nካፍ በቀጣዩ ዓመት የሚካሄደው የአፍሪካ ታላቁ የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለማዘጋጀት የተቸገረበት ዓመት ነበር። አሁን ባለው ሁኔታ ለ2019 የአፍሪካ ዋንጫ 13 አገራት ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።ይሁንና ከዝግጅት ማነስ ጋር በተያያዘ የአፍሪካ እግር ኳስ በበላይነት የሚመራው ተቋም መድረኩን የሚያዘጋጅለት አገር በማጣት ሲባክን ቆይቷል።ከዝግጅቱ ሂደት መዘግየት ጋር ተያይዞ ካፍ ለካሜሮን ተሰጥቶ የነበረውን የዘንድሮው የአፍሪካ ታላቅ የእግር ኳስ ሁነት የአዘጋጅነት ሚናን ነጥቋል።ይህንን ተከትሎም በአጭር ጊዜ ውስጥ ውድድሩን የማስተናገድ አቅምና ፍላጎት ያላቸው አገራት በማማተር ሲባክን ታይቷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2011ታምራት ተስፋዬ", "passage_id": "6ac1b2bd4b1f51a892636ab382aac5be" }, { "passage": "ይህ ሲሆን አልፍሬድ አይዠንስታድ የሚባል ዕድለኛ ፎቶ አንሺ ድንገት በቦታው ነበር። ቀጭ፣ ቀጭ፣ ቀጭ አደረገው፤ ካሜራውን።\n\nያ ፎቶ ሳር ቅጠሉን አነጋገረ። ዓለም ይህንን 'ድንገቴ መሳሳም' ወደደው። ሀውልትም ሠራለት። ስሙንም \"የማያዳግም ፍቅር\" ሲል ጠራው።\n\nትናንት ታዲያ በዚያ ፎቶ ላይ የልጅቱን ከንፈር ሲስም የሚየታው የያኔው ጎረምሳ 95 ዓመት 'ሞልቷቸው' ሞቱ።\n\nዓለም አዘነ። ስለዚያ ቅጽበታዊ ስሞሽም ይበልጥ መነጋገር ያዘ።\n\n• የዛሬ 74 ዓመት የተሳመው 'ከንፈር' ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ\n\n• ዓለም ሁሉ የሚያወራለት ክሪይፕቶከረንሲ ምንድነው? \n\nለካንስ አንዳንዶች ያን ሀውልት ሲያዩ ደማቸው ይፈላ ኖሯል። ለካንስ መሳሳሙንም እንደ ጾታዊ ጥቃት ነበር የሚመለከቱት። ሌሊቱን አድብተው ጥቃት አደረሱበት። ሀውልቱ ላይ። \n\nምነው ቢባሉ ያ 'መርከበኛ የልጅቱን ከንፈር የሳመው አስፈቅዶ ስለመሆኑ ምንም መረጃ የለም' አሉ።\n\nነሐሴ 14፤ 1945፤ ኒውዮርክ\n\nየ2ኛው የዓለም ጦርነት በአሜሪካ ድል አድራጊነት መጠናቀቁ በተበሰረበት ወቅት ነበር እነዚህ ሁለት ተአምረኛ ከንፈሮች የተገናኙት። \n\nእርግጥ ነው አይተዋወቁም። ተያይተውም ተደባብሰውም አያውቁም፣ ከዚያ በፊት። ያን ዕለት ግን ድንገት ተገናኙ። ያገናኛቸው ደግሞ የጃፓን በጦርነቱ እጅ መስጠት ነው።\n\nየአቶ ጆርጅ ማንዶሳ እና የወይዘሪት ዚመር ፈሬድማን ከንፈሮች ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ይኸው እስከዛሬ ዓለምን ጉድ አሰኝተዋል።።\n\nይህን ቅጽበታዊ ክስተት በፎቶ ካሜራ የቀለበው ዕድለኛ ሰው አልፍሬድ አይዠንስታድ ነው። እሱም \"አረ እኔ ድንገት ነው፣ አስቤበትም አይደለም ያነሳኋቸው\" ብሏል።\n\n• በካናዳ 7 ሕፃናት በእሳት ቃጠሎ ምክንያት ሞቱ\n\nፎቶው እጅግ ዝነኛና ዓለምን በአውደ ርዕይ ያዳረሰ ሲሆን ላለፉት 74 ዓመታት ዝናውን የነጠቀው የለም።\n\nይህ ሁሉ የሆነው ነሐሴ 14፣ 1945 ዓ.ም ነበር። \n\nታዲያ የትናንቱ ልብ የሚሰብረው ዜና በዚያ ፎቶ ላይ ይታይ የነበረው ያ የያኔው መርከበኛ በተወለደ በ95 ዓመቱ ከዚህ ዓለም መለየቱ ነበር።\n\nጥቃት አድራሾቹ ምን አሉ?\n\nበፍሎሪዳ ሳራሶታ የሚገኘው ይህ ሀውልት \"አንኮንዲሽናል ሰሬንደር\" የሚል ስም አለው። \"ለማይናወጽ ፍቅር እጅ መስጠት\" እንበለው? ወይስ \"የማያዳግም ፍቅር\"?\n\nይህን ሀውልት ያልታወቁ ሰዎች ሌሊቱን በቀለም አበለሻሽተውታል።\n\nበሀውልቱ ላይ በጎረምሳው መርከበኛ እየተሳመች ያለችው ወይዘሪት ዚመር እግሮቿ ላይ \"ሚቱ\"(Me too) የሚል ጽሑፍ በቀይ ቀለም ተጽፎባት ታይቷል። ይህም ምናልባት ድርጊቱ በ'አክራሪ ጾተኞች' የተፈጸመ እንደሆነ ጥርጣሬን አሳድሯል።\n\nፖሊስ የደረሰውን ጥፋት በገንዘብ አንድ ሺህ ዶላር ተምኖታል።\n\nለብዙዎች የነዚህ ጥንዶች 'ድንገቴ ስሞሽ' በወቅቱ የነበረውን መጠን ያለፈ ደስታና ፈንጠዚያ የሚወክል ነው። \n\nነገር ግን ክስተቱ በ'ጽንፈኛ ጾታ' ተሟጋቾች ዘንድ የተወደደ አይመስልም። የወቅቱን ፈንጠዚያ ከማሳየቱ ይልቅ ጾታዊ ጥቃትን ነው የሚዘክረው ብለው የሚሟገቱ አልጠፉም። \n\nይህን እንዲሉ ያስቻላቸው መርከበኛው መንዶሳ የወይዘሪት ፍሬድማንን ስምምነት ሳያገኝ ነው ከንፈሩን ከንፈሯ ላይ ያሳለፈው በሚል ነው።\n\nእርግጥ ነው ከዓመታት በፊት (በ92 ዓመታቸው) የያኔዋ ኮረዳ ወይዘሪት ዚመር ፍሬድማን በሰጠችው (በሰጡት) ቃል \"በ1945 ያ መርከበኛ የሳመኝ እኮ በፍቃዴ ሳይሆን እንዲያው ድንገት ደርሶ ጎተት አድርጎ ነበር ከንፈሬን የጎረሰው\" ሲሉ የወቅቱን ሁኔታ አስታውሰው ነበር። \n\nነገር ግን ይህን ቃል ሰጥተው በ2016 ሕይወታቸው ካለፈ በኋላ ልጃቸው ለኒውዮርክ ታይምስ እንደተናገረው እናቱ የያን ጊዜውን ድንገቴ ስሞሽ ያን ያህልም በአሉታዊ መንፈስ እንደማያዩት... ", "passage_id": "89f1518be1561d6150392fbad6e7cbb0" }, { "passage": "ጎልማሳው 25 ሜትር ከፍታ ባለው ለዚሁ ተግባር ተብሎ በተዘጋጀ ባላ ጫፍ ላይ በተቀመጠ በርሜል ላይ ለሁለት ወራት በመኖር ከዓለም ተወዳዳሪ የሌለው ግለሰብ ሆኗል። \n\nበዓለም ክብረወሰንነት ተይዞ የነበረው የተመሳሳይ ጀብዱ ክብረ ወሰን 54 ቀናት ነበር። ደቡብ አፍሪካዊዉ ክሩገር የዛሬዋን ሰኞ ጨምሮ 67 ቀናትን 'በርሜል መኖሪያዬ' ብሎ ምድርን ወደታች አቀርቅሮ እያየ ከርሟል። \n\nራሱን በርሜል ላይ ሰቅሎ በማቆየት ተወዳዳሪ ያልተገኘለት ጎልማሳው ከዚህ ቀደምም ከ22 ዓመት በፊት የነበረውን ክብረ ወሰን የሰበራው ራሱ ነበር። በ1997 (እ.አ.አ) ክብረ ወሰኑን አሻሽሎ 54 ቀናት ያደረገው ራሱ ቬርኖን ክሩገር ነበር።\n\nአሁን ክብረወሰኑን ያሻሻለበት በርሜል 500 ሊትር የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን አንድ ሜትር ከፍታና ግማሽ ሜትር ደግሞ የጎን ስፋት እንዳለው ክሩገር ተናግሯል። \n\nምግብን ጨምሮ ሁሉም የሚፈልገው ነገር በቅርጫት ታስሮ ይላክለታል፤ እርሱ ደግሞ ከላይ ሆኖ በገመድ በመጎተት በተላከለት ነገር የበርሜል ቤቱን ፍላጎት ያሟላል። \n\nበዚህ ሂደት ታዲያ አድናቂህ ነን ያሉ ግለሰቦች ለጊዜው ሚስጥር ያደረጋቸውን የተለያዩ ሰጦታዎች እንደሚልኩለት የተናገረው ክሩገር ከህጻናት የሚላኩ ከረሜላዎችን ሁሉ መቀበሉን ያስታውሳል። \n\nበርሜሉ ውስጥ መኖር ከጀመረ ከቀናት በኋላ ስፖርት የሚያሰሩት ሰዎች መኖራቸውን ገልጿል። \"ሁልጊዜ ጠዋት ሰዎች መጥተው ለግማሽ ሰዓት እራሴን እንዳፍታታ ያደርጉኛል\" ያለው ክሩገር ከዚያ በኋላ በአንጻሩም ቢሆን ኑሮ እንደቀለለለት ይናገራል።\n\nባላው በንፋስ ወቅት የተወሰነ ቢንቀሳቀስም ብዙም አያስፈራኝም ብሏል። ክሩገር እንደሚለው ልቡን በፍርሃት የሚያርደው ግን በደመና ወቅት የሚሰማው ከፍተኛ የመብረቅ ድምጽ ነው።\n\nበነእዚህ 67 ቀናት ውስጥ ታዲያ ለክሩገር ሁሉም ነገር ቀላል ባይባልም መፍትሔው ግን የሚከብድ አልነበረም። ከነገሮች ሁሉ ክሩገርን ያስቸገረው ጎኑን በእንቅልፍ ማሳረፍ አለመቻሉ እንደነበር ለቢቢሲ ተናግሯል።\n\n\"ምንም እግሬን መዘርጋት አልችልም፣ ጠርዙ ላይ ጋደም ማለት እፈልጋለሁ ግን እርሱም ስስ በመሆኑ ሲወጋኝ ያመኝና ወዲያውኑ እነቃለሁ\" በማለት ለመተኛት ይቸገር እንደነበር ገልጿል።\n\n ", "passage_id": "ce00d6a2fc6704fbdeb4c91f2d855592" }, { "passage": "ቦጋለ አበበበኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ለበርካታ ወራት ተቋርጠው የቆዩ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች ካለፈው ሐምሌ መጨረሻ ጀምሮ በሂደት ወደ መደበኛ መርሃግብራቸው እየተመለሱ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ውድድሮች በተመለሱበት ጥቂት ወራትም በተለይም የረጅም ርቀት የዓለም ክብረወሰኖች ለማመን በሚቸግር መልኩ ሲሰበሩ እየተስተዋለ ይገኛል፡፡ ይህም የስፖርቱን አፍቃሪዎች ከማነጋገሩ ባሻገር ተንታኞች ጭምር ግራ እንዲጋቡ ያደረገ ክስተት ሆኗል፡፡ በተለይም የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰን ከወረርሽኙ በፊትም ቢሆን ከሌሎች ርቀቶች በተለየ በሁለቱም ፆታ በተደጋጋሚ ሲሰበር መስተዋሉ አነጋጋሪ አድርጎታል፡፡ የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰን በዓለም አትሌቲክስ እኤአ ከ2004 አንስቶ እውቅና እየተሰጠው ከመጣ ወዲህ በወንዶች አምስትና በሴቶች ስድስት የዓለም ክብረወሰኖች ተመዝግበዋል፡፡ ከዚህ ዓመት በፊት በርቀቱ የተመዘገቡ ሰዓቶች በዓለም አትሌቲክስ ‹‹የዓለም ፈጣን ሰዓት›› በሚል ይታወቅ ነበር፡፡ የወንዶች ግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰን ባለፈው እሁድ በቫሌንሲያ የተመዘገበ ሲሆን ኬንያዊው አትሌት ኪቢዎት ኬንዲ 57፡32 በሆነ ሰዓት የክብረወሰኑ ባለቤት ሆኗል::የሴቶቹ ደግሞ ባለፈው የካቲት በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የራስ አል ኪማህ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አባብል የሻነህ በ1፡04፡31 በሆነ ሰዓት ያስመዘገበችው ነው፡፡ ይህም በጥቅምት 2017 ኬንያዊቷ ጆይስሊን ጂፕኮስጌ በቫሌንሲያ ግማሽ ማራቶን ካስመዘገበችው የቀድሞው የዓለም ክብረወሰን በሃያ ሰከንድ የተሻለ ነበር፡፡ በመስከረም 2019 ሌላኛዋ  ኬንያዊት\nብሪጊድ ኮስጌ በኒውካስትል ታላቁ\nሩጫ 64፡28 በሆነ ሰዓት\nከቀድሞው ክብረወሰን በሃያ ሦስት\nሰከንድ የተሻለ ፈጣን ሰዓት\nብታስመዘግብም የዓለም አትሌቲክስ ለክብረወሰኑ\nእውቅና አልሰጠውም። እኤአ ከ2011 ጀምሮ\nየዓለም አትሌቲክስ የሴቶች ግማሽ\nማራቶን ክብረወሰኖችን በሴትና በወንድ አሯሯጭ\nየተመዘገቡ ብሎ በሁለት ከፍሏቸዋል።  በሴት\nአሯሯጮች የተመዘገበው የርቀቱ ክብረወሰንም በኬንያዊቷ\nአትሌት ፔርስ ጂፕቺርቺር 1፡05፡16 በሆነ ሰዓት\nከወር በፊት በፖላንድ ጊዲኒያ\nየዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና\nየተመዘገበ ነው። ባለፈው ሐምሌ መጨረሻ ለአስራ ስድስት ዓመታት ያልተደፈረው የቀነኒሳ በቀለ የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን በዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሞናኮ ላይ ከተሰበረ ወዲህ የዓለም ክብረወሰኖች በተለይም በረጅም ርቀት ውድድሮች እንደልብ የሚሰበሩ ሆነዋል። ከዩጋዳዊው ያልተጠበቀ ክብረወሰን በኋላ አንድ ወር ባልሞላ ልዩነት ትውልደ ሶማሊያዊው የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ እኤአ 2007 ላይ በጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ተይዞ የቆየው ‹የአንድ ሰዓት ውድድር› የዓለም ክብረወሰን ብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ላይ ከ21፡330 ወደ 21፡285 ተሻሽሏል። በተመሳሳይ ርቀት እንዲሁም በተመሳሳይ ቀንና ውድድር በኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድሬ ቱኔ 18፡930 ተይዞ የቆየው የዓለም ክብረወሰን በትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን 18፡517 በሆነ ሰዓት ተሻሽሏል። የሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአንድ ሰዓት ውድድር የዓለም ክብረወሰኖች በተሰበሩ በአንድ ወር ልዩነት ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ለአስራ አምስት ዓመታት ያልተደፈረውን የቀነኒሳ በቀለ የአስር ሺ ሜትር ክብረወሰን በ6፡53 ሰከንድ መስበር ችሏል። በተመሳሳይ ቀን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌትና የረጅም ርቀት ንግስት ጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት ተይዞ ሳይሰበር የቆየውን የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን 14፡06 በሆነ ሰዓት ሰብራዋለች። ኬንያውያን አትሌቶችም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኋላ ባንሰራራው የአትሌቲክስ ውድድር የክብረወሰን ተቋዳሽ ናቸው። ለዚህም በዓለም ግማሽ ማራቶን በአርባ ሁለት ቀናት ልዩነት ሁለት የዓለም ክብረወሰኖችን የጨበጠችው ኬንያዊቷ ፔስር ጂፕቺርቺር ትክክለኛ ማሳይ ናት። መስከረም ላይ በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን የሴቶችን ብቻ የርቀቱን የዓለም ክብረወሰን በ1፡05፡24 ሰዓት ያሻሻለችው ኬንያዊት አትሌት ከአርባ ሁለት ቀናት በኋላ በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የራሷን ክብረወሰን በአስራ ስምንት ሰከንድ ማሻሻል ችላለች። እነዚህ ሁሉ ክብረወሰኖች ሲሰባበሩና አትሌቶች በተለየ መልኩ አስደናቂ ብቃት ሲያሳዩ አብዛኛው የስፖርት ቤተሰብ ሁለት ነገሮችን ጠርጥሯል። ይህም በወረርሽኙ ምክንያት አትሌቶች ለረጅም ጊዜ ከውድድር በመራቃቸው ሰፊ የዝግጅት ጊዜ በማግኘት ወደ ውድድር ሲመለሱ ምርጥ ብቃት ሊኖራቸው እንደቻለና በነዚያ የረፍት ጊዜያት በጉዳት ላይ የነበሩ አትሌቶች በበቂ ሁኔታ ማገገም በመቻላቸው እንደሆነ ይታሰባል። ስፖርቱን በጥልቀት የሚመለከቱ በርካታ ተንታኞች ግን ከዚህም የበለጡ ገፊ ምክንያቶች ከክብረወሰኖቹ መሰባበር ጀርባ እንዳሉ ያምናሉ። የልምምድ ስነልቦናና ሂደት በወረርሽኙ ምክንያት እየተለወጠ መምጣቱ ለክብረወሰኖቹ መሻሻል አንድ ምክንያት ተደርጎ ይወሰዳል። ይህም የወረርሽኙ ስጋት ቀደም ብሎ አትሌቶች በርከት ብለው በአንድ አሰልጣኝና በአንድ ካምፕ ውስጥ ሆነው የሚያደርጉትን የተለመደ ዝግጅት ወደ ጎን ትተው በተናጠል በሚመቻቸው ስፍራና በቤታቸው ሆነው እንዲዘጋጁ እድል መስጠቱ ነው። ይህ አጋጣሚ አትሌቶች አንዱ አንዱን ሳይጠብቅ በራሳቸው መርሃግብር መሰረት ወጥ በሆነ መልኩ እስከ አቅማቸው ጥግ ድረስ እንዲዘጋጁ ያስቻላቸው ሲሆን በስነልቦናውም ረገድ ጠንካራ እንዲሆኑ አድርጓል። ለዚህም ከወረርሽኙ በኋላ ክብረወሰኖችን ያሻሻሉ አትሌቶች ቀደም ሲል ይከተሉት የነበረው የልምምድ መልክ በወረርሽኙ ሳቢያ መቀየሩ ለክብረወሰኖች መሻሻል ቁልፍ ሚና እንዳለው የሚያስቀምጡ ባለሙያዎች በርካታ ናቸው። በሌላ መልኩ አትሌቶች በወረርሽኝ ምክንያት ውድድሮች ቢቆሙም የሆነ ጊዜ ላይ እንደሚቀጥሉ አውቀው ዝግጅታቸውን ሳያቋርጡ ተግተው መስራታቸው የክብረወሰን ባለቤት እንዳደረጋቸው ይታመናል። አትሌቶች ወረርሽኙ የጤና ስጋት ቢሆንም መጥፎን አጋጣሚ ወደ ጥሩ ለውጠው ተጠቅመዋል። አቋማቸው እንዳይወርድ በመጠንቀቅ መዘጋጀታቸው ኋላ ላይ ለስኬት አብቅቷቸዋል። በተለይም እቤት የመቀመጥ አስገዳጅ ሁኔታው ቀደም ሲል የነበረባቸውን የተጣበበ የልምምድና የውድድር ጫና በማስቀረቱ በበቂ ሁኔታ እንዲዘጋጁ በር ስለከፈተላቸው በደህናው ጊዜ ማሳካት ያልቻሉትን ክብረወሰን እንዲያሳኩ አድርጓቸዋል። ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ መልካም አጋጣሚዎች እንዳሉ ሆነው የስፖርት ቴክኖሎጂ እየዘመነ መምጣት ለተመዘገቡት ክብረወሰኖች የአንበሳውን ድርሻ እንደሚይዝም ዓለም አቀፍ የስፖርቱ ምሁራን የሚስማሙበት ጉዳይ ነው። ባለፉት ጥቂት ወራት ሲመዘገቡ ያየናቸው በርካታ ክብረወሰኖች አትሌቶች የሚያስመዘግቧቸው ሰዓቶች ላይ ሰፊ ልዩነት በሚፈጥሩ ዘመናዊ የመሮጫ ጫማ እንዲሁም አሯሯጮች በተለይም በመም ውድድሮች ከሰው ይልቅ ቴክኖሎጂ ሆኖ አትሌቶችን እስከ መጨረሻ ድረስ በሚፈለገው ደረጃ በማገዝ የተመዘገቡ ናቸው። ግዙፉ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚያቀርባቸው የመሮጫ ጫማዎች ቀደም ሲል የዓለም ክብረወሰን ሲመዘገብባቸው ከቆዩ የመሮጫ ጫማዎች አንፃር በአትሌቶች ፍጥነት ላይ የጎላ ተፅዕኖ እንዳላቸው አትሌቶችም ይሁን የስፖርት ቤተሰቡ ይስማማሉ። ከዚህ በላይ የጥሩነሽ ዲባባ የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ለተሰንበት ግደይ እና የቀነኒሳ በቀለ የአምስትና አስር ሺ ሜትር ክብረወሰኖች በዩጋዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሲሰበሩ አትሌቶቹን በአሯሯጭነት ያገዛቸው በመሮጫው መም ዙሪያ የተገጠመው መብራት(Wave-lights) እንደነበር ይታወቃል። ይህ ቴክኖሎጂ አትሌቶቹ በምን ያህል ፍጥነት እያንዳንዱን ዙር ሮጠው ክብረወሰን እንደሚጨብጡ አስልቶ በማሯሯጥ እስከ መጨረሻ ድረስ ደግፏቸዋል። አሯሯጭ በአትሌቲክሱ ዓለም ክብረወሰኖችን ለማስመዝገብ ወሳኙ ነገር እንደሆነ ይታወቃል። አንዳንድ ጊዜ ሴት አትሌቶች በወንድ አሯሯጮች ታግዘውም አሯሯጮች በሚፈለገው ፍጥነት መጓዝ ካልቻሉ ክብረወሰን የማይሰበርበት አጋጣሚ ጥቂት እንዳልሆነ ይታወቃል። አሯሯጩ ቴክኖሎጂ ሆኖ እስከ መጨረሻ ድረስ ወጥ በሆነ ስሌት አትሌቶችን ሲያግዝ ግን የተለየ እንደሚሆን የቅርቦቹ ክብረወሰኖች ምስክር ናቸው።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 5/2013 ", "passage_id": "bd9d938962843a2319cf059722b904bd" }, { "passage": "ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአትሌቲክሱ ዓለም በተለይም በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች ትኩረት እያገኘ የመጣው ወጣት አትሌት ሰለሞን ባረጋ የስኬት ማማ ላይ ለመቆም ብዙ ጊዜ አልወሰደ በትም። ከዕድሜው ከፍ ብሎ ከታላላቆቹ ጋር በመፎካከርም በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ለማመን የሚከብዱ ድሎችን አጣጥሟል። ይህም በረጅም ርቀት በተለይም በአምስት ሺ ሜትር ኢትዮጵያ ከነ ቀነኒሳ በቀለ ወዲህ ማግኘት ያልቻለችውን ሁነኛ ተተኪ አትሌት በቅርቡ ልታገኝ እንደምትችል ፍንጭ የሰጠ መሆኑን የስፖርቱ ባለሙያዎች ሲናገሩ ይደመጣል።በዳይመንድ ሊግ ተሳትፎው ገና በሁለተኛ ዓመቱ የአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ አሸናፊ መሆን የቻለው ሰለሞን ዕድሜው አስራ ሰባት ዓመት ቢሆንም በልምድ የሚበልጡትን አትሌቶች የሚያስንቅ የሩጫ ተሰጥኦ እንዳለው በተለያዩ አጋጣሚዎች ማሳየት ችሏል። 2018 የውድድር ዓመትም ስኬታማ የሆነበት ነው ማለት ይቻላል። ይህም እ.ኤ.አ ከ2011 ወዲህ አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት በዓለም የዓመቱ ኮከብ አትሌቶች ምርጫ ከአስሮቹ እጩዎች ውስጥ እንኳን ባልተካተቱበት ሁኔታ ሰለሞን በወጣቶች ዘርፍ ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች መካከል አንዱ እንዲሆን አስችሎታል። ሽልማቱን የማሸነፍ ሰፊ ዕድል እንደሚኖረውም ይጠበቃል።የደቡብ ፖሊሱ ክለብ አትሌት የሆነው ሰለሞን ባረጋ እያስመዘገበ ላለው ስኬት ከሁለት ወራት በፊት ክለቡ የኢንስፔክተርነት ማዕረግ የሰጠው ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት እያሳየ ያለው አስደናቂ ብቃት ወደ ፊት ተስፋ እንዲጣልበት አድርጓል። በ2018 የውድድር ዓመት የአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊ ሲሆን በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች የዓለም ክብረወሰንን 12፡43፡02 በሆነ ሰዓት ከመጨበጡ ባሻገር እ.ኤ.አ 2005 ላይ ቀነኒሳ በቀለ በርቀቱ ካስመዘገበው ሰዓት ወዲህ ፈጣን ሰዓት መሆኑ ይታወሳል። ሰለሞን በዓለም ከሃያ ዓመት በታች ቻምፒዮናና በአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮናም በርቀቱ አራተኛ ደረጃን ይዞ በመፈፀም በውድድር ዓመቱ በርካታ ስኬቶችን አግኝቷል። ይህንንም በተመለከተ ከዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ድረ ገፅ ጋር ሰሞኑን ቃለ መጠይቅ አድርጓል።የ2018 የውድድር ዓመት ልምምዱን ሲጀምር ከውድድሮች ይልቅ ልምምዱ ላይ ትኩረት አድርጎ በተለየ መንገድ ለመሥራት ከአሰልጣኞቹ ጋር እንደተስማማ የሚናገረው ሰለሞን በውድድር ዓመቱ የተለየ ብቃት ለማሳየቱ ምክኒያቱ ይህ መሆኑን ይናገራል።ሰለሞን በውድድር ዓመቱ በቤት ውስጥና ከቤት ውጭ ውድድሮች አስደናቂ ብቃት ቢያሳይም በብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ፈጣን የተባለውን 12፡43፡02 ሰዓት ለመሮጥ እንዳላሰበ ያብራራል። ይሁን እንጂ ይህን ጣፋጭ ድል የግሉ ካደረገ በኋላ ሰዓቱን ሲመለከተው ለማመን ተቸግሮ እንደነበር አልሸሸገም። «የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ መሆን ለእኔ አስገራሚ ስኬት ነው፤ ይህን ሰዓት ማስመዝገብ ደግሞ ፈፅሞ ሊታመን የማይችል ነበር» ያለው ወጣቱ አትሌት ይህ የሩጫ ዘመኑ ሁሉ ትልቅ ስኬት እንደሆነ ይናገራል።ቀደም ሲል በአምስት ሺ ሜትር ከነበረው የራሱ ምርጥ ሰዓት 12፡55 በታች መሮጥ የሁል ጊዜም ፍላጎቱ እንደሆነ የሚናገረው ሰለሞን 12፡43 በሆነ ሰዓት ርቀቱን ማጠናቀቅ መቻሉ ሁሉንም ነገር እንደቀየረው ያስረዳል። ይህም ከአስራ አምስት ዓመታት በላይ በቀነኒሳ በቀለ ተይዞ የቆየውን የአምስት ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን አንድ ቀን በእጁ ለማስገባት ጠንክሮ እንዲሠራ እንዳነሳሳው ያብራራል።ከ18 እና ከ2o ዓመት በታች የዓለም ወጣቶች ቻምፒዮና አሸናፊ መሆን የቻለው ሰለሞን ባለፈው የለንደን የዓለም ቻምፒዮና በቀጥታ ወደ ትልቅ ደረጃ ተሸጋግሮ የኢትዮጵያውያንን የአምስት ሺ ሜትር ስብስብ ምን ያህል አስፈሪ እንዳደረገው ይታወሳል፡፡በሁለት ኦሊምፒኮችና በሦስት የዓለም ቻምፒዮናዎች ኢትዮጵያ በሞ ፋራ የተነጠቀችውን የአምስት ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያ ለንደን ላይ በሙክታር ኢድሪስ አማካኝነት ስታስመልስ የሰለሞን ሚና ቁልፍ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በበርሚንግሃሙ የዓለም ቻምፒዮና ዮሚፍ ወርቅ ባጠለቀበት ውድድር ሰለሞን የብር ሜዳሊያ ባለቤት በመሆን ያሳየው ድንቅ አቋም በቀጣይ ዓለም አቀፍ መድረኮች ከመካከለኛ እስከ ረጅም ርቀቶች ኢትዮጵያውያን የበላይነታቸው ከወዲሁ ጎህ እየቀደደ እንደሚገኝ ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነው። ", "passage_id": "bd110c2c1109e57dd88bc098cb65051a" } ]
4aa72dafd11dcd7ab9559c9e03a02ab6
da5347c7846a191a2cef7948bae9c650
ብልጽግና በንጹሃን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ የሚፈጸምን ጥቃት አወገዘ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ብልጽግና ፓርቲ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ በንጹሃን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት በማድረግ እየተካሄደ ያለውን ጥቃት አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገለጸ።ፓርቲው እንዳስታወቀው፤ ዜጎችን በማንነት ለይቶ በማጥቃት ምንም አይነት የፖለቲካ ትርፍ ሊገኝ አይችልም። በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተደጋጋሚ በዜጎች ላይ እየተካሄደ ያለው ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት የትኛውንም የሕዝብ ክፍል የማይወክልና ኃላፊነት የማይሰማቸው የግጭት ነጋዴዎች ሴራ መሆኑን መላው የሀገራችን ሕዝቦች ሊገነዘቡ ይገባል።በጨካኝ አረመኔ የጥፋት ኃይሎች ጥቃት በንጹሃን ዜጎች ላይ እየደረሰ ላለው ጉዳት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸን ለዘመናት ተከባብሮ ክፉና ደጉን አብሮ ያሳለፈን ህዝብ በማጋጨት ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚጣጣሩ የውስጥም ሆነ የውጭ ኃይሎች የማይሳካላቸው መሆኑን አጥብቀን ልንገልጽላቸው እንወዳለን።በዜጎች ላይ እየደረሰ ባለው ጥቃት ውስጥ ተሳትፎ ያላቸውንና ችግሩ እንዲፈታ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ባልተወጡ የስራ ኃላፊዎች ላይ ጥብቅ ፖለቲካዊ፣ ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እንገልጻለን።ምንም አይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን ለፍቶ አዳሪ ንጹሃን ዜጎችን በማንነታቸው ብቻ ለይቶ በማጥቃት ሀገርንና ሕዝብን ወደ ትርምስ ለማስገባት ተቀናጅተው የሚንቀሳቀሱ የውስጥም ሆነ የውጭ ጨካኝ የጥፋት ኃይሎችን አጥብቆ የሚያወግዝና በእነዚህ ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዶ የዜጎች ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ ብልጽግና ፓርቲ አጥብቆ የሚታገል መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38084
[ { "passage": "አዲስ አበባ ፣ህዳር 7 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሀገር የካደውን የህወሓት የጥፋት ቡድን የሚያወግዝ ሰልፍ በተለያዩ አካባቢዎች ተካሄደ፡፡በዚህም በጋምቤላ፣ በቡሌ ሆራ፣ በሆሳዕና ከተሞች የህወሓት ጽንፈኛ ቡድን በሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝ ላይ የፈፀመውን ጥቃት የሚያወግዙ ሰልፎች ተካሄደዋል።የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች የህወሓት ጁንታ እያካሄደ ያለውን ሀገር የማፍረስ ዓላማ ለማስቆም እና ወንጀለኞችን ለህግ ለማቅረብ የመከላከያ ሰራዊት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉ ጠቁመው ከሰራዊቱ ጎን በመሆን አስፈላጊውን ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡አሸባሪው የህወሓት ቡድን ተስፋ የቆረጠ የጥፋት ቡድን በመሆኑ በተለያዩ አካባቢዎች ባሰማራቸው ቡድኖች ጥቃት ሊፈጽም ስለሚችል የጋምቤላ ክልል ህዝብ ከፀጥታ አካሉ ጋር በመሆን አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅ አስገንዝበዋል፡፡በድጋፍ ሰልፉ ማጠናቀቂያ ላይ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የደም ልገሳ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡በተመሳሳይ ዜናም በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ጉጂ ዞን የቡሌ ሆራ ከተማ ነዋሪዎች እና የቡሌ ሆራ ወረዳ ነዋሪዎች በዛሬው ዕለት በቡሌ ሆራ ከተማ ባደረጉት ሰላማዊ ሰልፍ ፅንፈኛው የሕወሓት ቡድን በመከላከያ ሠራዊት የሰሜን እዝ ላይ ያደረሰውን ጥቃት እንደሚያወግዙ ገልጸዋል፡፡ነዋሪዎቹ ከድጋፍ ሰልፉ ባሻገር ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ከ200 በላይ ሰንጋዎች እና ከ1 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ብር ድጋፍ በማድረግ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን አጋርነት አሳይተዋል።በተመሳሳይ ሁኔታ ሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች የሕወሓት ቡድን የፈፀመውን የሀገር ክህደት የሚያወግዝ ሕዝባዊ ሰልፍ በሐዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ አካሂደዋል።አረመኔው የጥፋት ቡድን ሀገር ለማፍረስ የሚንቀሳቀስ ጠላት መሆኑን በማውገዝ መንግሥት እየወሰደ ያለውን ሕግ የማስከበር እርምጃ እንደሚደግፉ የሰልፉ ተሳታፊዎች አስታውቀዋል።የሰልፉ ተሳታፊዎች ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን መሆናቸውንም ነው የገለጹት፡፡የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲም በትግራይ የህግ ማስከበር ዘመቻ እያካሄደ ለሚገኘው የአገር መከላከያ ሰራዊት ግምታቸው 680 ሺህ ብር የሆኑ 200 ፍየሎች እና የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "4658208c8ac0bf1d12aabd06fde8d0b2" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መጋቢት 1፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያውያንን አብሮነት ሊሸረሽሩ የሚችሉ የጥላቻ ንግግሮችን በሚያሰራጩ አካላት ላይ መንግስት ተገቢውን እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች አሳሰቡ።ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የጥላቻ ንግግሮችን በሚያስተላልፉ አካላት እና መወሰድ በሚገባቸው እርምጃዎች ዙሪያ ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፣ ከትግራይ ዴሞክራሲ ትብብር ፓርቲ (ትዴትፓ) እና ከሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ፓርቲ አመራሮች ጋር ቆይታ አድርጓል።የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ቀጄላ መርዳሳ፥ የጥላቻ ንግግሮችን ለመቆጣጠር በወጣው ህግ መሰረት መሰል ድርጊቶችን የሚፈጽሙ አካላት ላይ አስተማሪ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል።የጥላቻ ንግገሮችን እና ሃሰተኛ መረጃዎችን የሚያሰራጩ መገናኛ ብዙሃን ላይ የሚደረገው የቁጥጥር ስራ ሊጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል።የትግራይ ዴሞክራሲ ትብብር ፓርቲ (ትዴትፓ) ሊቀ መንበር ዶክተር አረጋዊ በርሄ በበኩላቸው፥ ዋልታረገጥ የሆነ አመለካከት እውነታውን ካለመገንዘብ የሚመነጭ ስህተት መሆኑን አብራርተዋል።እነዚህ የጥላቻ ንግግሮች የማህበረሰቡን የእርስ በርስ መስተጋብር ጥርጣሬ ውስጥ በመክተት ልዩነትን የማስፋት ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑንም አውስተዋል።ስለሆነም መሰል የጥላቻ ንግግሮች እና ሃሰተኛ መረጃዎችን የሚያሰራጩ አካላት በተገቢው ሁኔታ ተለይተው በህግ ሊጠየቁ ይገባል ነው ያሉት።በተለያዩ ህዝባዊ መድረኮች ላይ የሚተላለፉ መልዕክቶችን የመቆጣጠሩ ሂደት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባም ተናግረዋል።የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ሊቀ መንበር አቶ ዱካሌ ላሚሶ፥ በየትኛውም ሁኔታ የሚሰራጩ የጥላቻ ንግግሮች እና ሀሰተኛ መረጃዎች ህዝብን ለማጋጨት ያለሙ መሆናቸውን ይናገራሉ።\nየፖለቲካ ፓርቲዎቹ መሰል መልዕክቶች የኢትዮጵያውያን አብሮ የመኖር ባህል እና የህዝቡን አንድነት ብሎም ግንኙነት የሚሸረሽሩ በመሆኑ መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባ አሳስበዋል።አመራሮቹ የህዝቡን አንድነት ሊያጠናክሩ በሚገቡ ተግባራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።በሃይለኢየሱስ መኮንን", "passage_id": "350c0b5862dfc84709fa16bf26877d7f" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በጋምቤላ ክልል የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በህወሃት ውስጥ ያለ ቡድን በመከላከያ ላይ የፈፀመውን ጥቃት አውግዘዋል።", "passage_id": "1d4e66b316c84473e983a00529dbe7ac" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትናንትናው ምሽት ባወጣው መግለጫ በቦታው የነበረው የፌደራል ወታደሮች መውጣታቸውን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በምእራብ ወለጋ በጋዋ ካንካ፣ በጊላጎጎላና በሴካ ጅርቢ ቀበሌዎች 60 አባላት ባሉት ቡድን ግድያ መፈጸሙን ከአካባቢው ምንጮች ማግኘቱን አስታውቋል፡፡\nኢሰመኮ የፌደራልና የክልል መንግስታት በግድያው ላይ በአፋጣኝ ምርመራ እንዲጀምሩና፣ ለጥቃት ተጋላጭ መሆኑ ለረጅም ጊዜ ከሚታወቀው ቦታ ሰራዊቱ እንዲወጣ የተደረገበት የጀርባ ምክንያት እንዲታወቅና የሰላማዊ ዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ተመጣጣኝ እርምጃ እንዲወስድ አሳስቧል፡፡\nመግለጫው“ አጥቂዎቹ በሶስቱ ቀበሌዎች የሚኖሩ አማራዎችን አላማ አድርገዋል፡፡ ኢስመኮ ባገኘው መረጃ የተገደሉት ሰዎች ከቤታቸው ተወስደው ትምህርት ቤት ውስጥ ነው፡፡ “\nመንግስት በጥቃቱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 32 ነው ቢልም ኢሰመኮ ግን አገኘሁት ባለው የመጀመሪያ ምርመራ ከዚህ በላይ ሊሆን ይችላል ብሏል፡፡\nየኢስመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳኒኤል በቀለ እንዳሉት የንጹሃኑ ግድያ እጅግ ዘግናኝና የሰብአዊነት መርህን የጣሰ መሆኑን ተናግረዋል፡፡\n“የቱንም ያህል ሀዘን ጭካኔውን ምክንያታዊ ሊያደርግ አይችልም፤ጥቃት አድራሾች ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል” ብለዋል ኮሚሽነሩ፡፡\nህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ ሰለባ በሆኑበት ጥቃት የፌደራል የክልል መንግስታት በቦታው ይንቀሳቀሳል የሚባለውን ኦነግ ሽኔ ተጠያቂ አድርገዋል፡፡\nእሁድ እለት የተፈጸውን ግድያ የኦሮሚያ ክልል የሽብር ድርጊት ነው ባለው ጥቃት ንጹሀን ሰለባ መሆናቸውን ቀደም ብሎ መግለጹ ይታወሳል፡፡ የአማራ ክልል በበኩሉ ንጹሃን አማራዎች መገደላቸውን ገልጾ ግድያውን አውግዟል፡፡\nጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ማንነትን መሰረት ባደረገው ጥቃት እንዳዘኑ ገልጸው፤ ጥቃት አድራሾች ላይ እርምጃ ለመውሰድ የመከላከያ ኃይል ወደ ቦታው መሰማራቱን አስታውቀዋል፡፡\n", "passage_id": "bacb6c1f93fa035a87859e50474567a2" }, { "passage": "ፀረ ሰላም ኃይሎች ባላቸው አካላት በዜጎች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን መንግሥት በአስቸኳይ እንዲያስቆመው የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ጠየቀ፡፡ ወንጀለኞቹ በሕግ እንዲጠየቁም ጥሪ አቀረበ፡፡ ", "passage_id": "e58d8a7fec2a7d360c1c1e95242b8cd0" } ]
d1e15d22339035d6f2c85f6fa3da96d3
10899382e3f1a02bc48ef67ccba14e9f
የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች የኮቪድ-19 የሕይወት ኢንሹራንስ ሊገባላቸው ነው
ፍሬህይወት አወቀአዲስ አበባ፡- ኮቪድ-19 ወረርሽኝ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ተከትሎ ለድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች እና ለረዳት አሽከርካሪዎች የሕይወት ኢንሹራንስ ሊገባላቸው መሆኑን የኢፌዴሪ ትራንስፖርት ሚኒስቴር የመድን ፈንድ አስተዳደር ኤጀንሲ ገለጸ።የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ወርቅነሽ ብሩ ትናንት በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ኤጀንሲው ለበሽታው ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ አሽከርካሪዎችና ረዳቶች የሕይወት ኢንሹራንስ እንዲኖራቸው ከባለድርሻዎች ጋር ሰፋፊ ውይይቶችን ሲያደርግ የቆየ ሲሆን፤ በዚህም መሰረት ድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎችና ረዳት አሽከርካሪዎች በኮቪድ 19 ምክንያት ለሚደርስባቸው ጉዳት የሕይወት ኢንሹራንስ ሊገባላቸው ነው።እንደ ወይዘሮ ወርቅነሽ ማብራሪያ፤ አሽከርካሪዎች በወረርሽኙ ቢጠቁ ከኢንሹራንስ አንጻር ህብረተሰቡን እንዴት መጥቀምና መደገፍ ይቻላል የሚለውን በተለያየ መንገድ ማየትና መደገፍ አስፈላጊ እንደሆነ ታምኖበታል።የሕይወት ኢንሹራንሱ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ ሚና ያላቸውና ከሀገር ውስጥ ወደ ውጭ ሀገር ከውጭ ሀገር ወደ ሀገር ውስጥ የተለያዩ ምርቶችን የሚያመላልሱ ሾፌሮችን ያለስጋት እንዲንቀሳቀሱ ያስችላል።ሹፌሮችና ረዳቶች በስራቸው በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለወረርሽኙ ተጋላጭ በመሆናቸው የተለያዩ መገለሎች የሚደርስባቸው መሆኑ ያነሱት ዋና ዳይሬክተሯ፤ የሕይወት ኢንሹራንሱ መገባቱ ወሳኝ መሆኑን ያስረዱት ወይዘሮ ወርቅነሽ፤ ሾፌሮች ለሚያስተዳድሯቸው የቤተሰብ አባላትም ዋስትና እንደሚሆን ገልጸዋል። ሹፌሮችም ሆኑ ረዳቶች ዋስትና ያላቸው መሆኑን በመረዳት ስራቸውን በልበ ሙሉነት እንዲወጡ ያስችላቸዋልም ብለዋል።በወረርሽኙ ስርጭት ምክንያት የተቀነሱ በርካታ ረዳቶች መኖራቸውን የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሯ፤ ሾፌሮች ብቻ ወደ ጅቡቲ ወደብ የሚገቡ መሆኑን ተናግረው የሕይወት ኢንሹራንስ መገባቱ ረዳቶቹንም ሆነ ስራ ፈተው የተቀመጡ ሹፌሮችን ወደ ስራቸው እንዲመለሱ ያደርጋል ብለዋል።ሹፌሮችና ረዳቶች ያለስጋት መስራት ከቻሉ ባለንብረቶችም ተጠቃሚ ይሆናሉ ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፤ በሀገሪቱ ያሉት የኢንሹራንስ ኩባንያዎች በተለይም በሕይወት ኢንሹራንስ ብዙ ልምድ የሌላቸው በመሆናቸው በህብረተሰቡ ውስጥ ሰርጸው እንዲገቡና እንዲታወቁ ዕድል የሚፈጥርላቸው መሆኑን አመልክተዋል። ከሚፈጥርላቸው ጥሩ አጋጣሚ ባለፈም ወደፊት ቀጣይነት ባለው መንገድ ከድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች በተጨማሪ ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎችም እንዲቀላቀሉት ያደርጋል። ከዚህም ባሻገር የኢንሹራንስ ኩባንያዎቻችን እያደጉ ሄደው ለሀገሪቱ ትልቅ አቅም መፍጠር የሚችሉ ኢንዱስትሪዎች እንደሚሆኑም ተናግረዋል። ለድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች የሕይወት ኢንሹራንስ በመስጠት ተባባሪ የሆኑት የመድህን ፈንድ አስተዳደር ኤጀንሲ፣ የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን፣ የኢንሹራንስ ኩባንያዎችና የድንበር ተሸጋሪ ተሽከርካሪ ባለንብረቶች ማህበራት መሆናቸውን የገለጹት የኢትዮጵያ መድህን ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚና የኢትዮጵያ መድህን ሰጪዎች ማህበር ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ነጻነት ለሜሳ፤ አሽከርካሪዎችና ረዳቶች በኮቪድ 19 ምክንያት ሞትና ስራ የማቋረጥ አደጋ ቢደርስባቸው ቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን ለማቃለል ያለመ ተግባር መሆኑን አመልክተዋል። ኢንሹራንስ ኩባንያዎች ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን በመወጣት ለሾፌሮችና ለረዳቶቻቸው ሊከፈል ከሚገባው የአረቦን መጠን 50 በመቶ ብቻ እንዲከፍሉ ያደረጉ ሲሆን ቀሪውን 50 በመቶ ደግሞ የተሽከርካሪዎች ባለንብረቶች እንዲከፍሉ ማድረጋቸውንም ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል። በዓመት የሚከፈል የአረቦን መጠን ለእያንዳንዳቸው በነፍስ ወከፍ ለሾፌር 2046 ብር ከስድስት ሳንቲም ሲሆን ለረዳቶች ደግሞ 754 ብር ከሃምሳ ሳንቲም ይከፈላል። በቫይረሱ ምክንያት የሞት አደጋ ሲደርስባቸው ለሾፌር 250 ሺ ብር ለረዳት ደግሞ 150 ሺ ብር የሚከፈል መሆኑን አቶ ነጻነት ገልጸው፤ በተጨማሪም በኮቪድ ምክንያት ታሞ ለሁለት ወራት ስራ ካቋረጠ ለሾፌር ስድስት ሺ ብር ለረዳት ደግሞ ሶስት ሺ ብር የሚከፈል መሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሰሪዎች ፌዴሬሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደጀኔ ሉጬ በበኩላቸው፤ እንደ ትራንስፖርት ሚኒስቴር ኮቪድ 19ኝ በህብረተሰቡ ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመከላከል የተለያዩ ስራዎች እንደተሰሩ አስታውሰው፤ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች አደጋ ከደረሰ በኋላ ሰዎችን ለመርዳት ከመሄድ ይልቅ አስፈላጊውን በጀት መድበው በቅድመ ጥንቃቄ ላይ ቢሰሩ የተሻለ መሆኑን ተናግረዋል። ከሕይወት ኢንሹራንስ ጋር ተያይዞም ቫይረሱ ባህሪውን እየቀያየረና እየተስፋፋ የመጣ በመሆኑ የሾፌሮችን ደህንነት መጠበቅ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው፤ ሾፌሮች ከዚህ ቀደም በተለያዩ መድረኮች በተደጋጋሚ ሲያነሱት የነበረ ጥያቄ መሆኑንም ተናግረዋል።ለሾፌሮችና ለረዳቶች የሕይወት ኢንሹራንስ መገባቱ አስፈላጊና ወሳኝ ነው ያሉት አቶ ደጀኔ፤ አሽከርካሪዎች እየተሳቀቁ መጓዝ የሌለባቸው መሆኑን ገልጸው እያንዳንዱ ባለድርሻ አካላትም ለተግባራዊነቱ የበኩሉን መወጣት እንደሚገባ አመልክተዋል። በሀገሪቱ ከፍተኛ የሆነ የአሽከርካሪዎች እጥረት መኖሩን የገለጹት አቶ ደጀኔ፤ ያሉትን ሾፌሮች በአደጋና በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ማጣት የለብንም። አሽከርካሪዎች የኢትዮጵያ ወደቦች እንደመሆናቸው ሾፌሮችን በአደጋ የምናጣ ከሆነ ወደብ አይኖረንም። ስለዚህ ወደብ ሆነው እያገለገሉ ላሉት ሾፌሮች ልዩ ትኩረት መስጠት አስፈላጊ ነው ሲሉም ተናግረዋል።የሕይወት ኢንሹራንሱን ያቀላጥፋሉ ተብለው የሚታሰቡት ማህበራት በመሆናቸውና ማህበራት ደግሞ ከአደረጃጀት መመሪያ ጋር ተያይዞ የመፍረስ አደጋ ውስጥ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ ደጀኔ፤ ለዚህም አሰሪዎች ራሳቸው የህይወት ኢንሹራንሱን ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩና ትብብር እንዲያደርጉም ጥሪ አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38070
[ { "passage": "“የሦስተኛ ወገን መድን ዋስትና ካልለጠፍን ስምሪት አይሰጠንም፡፡” አሽከርካሪ“በኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተሽከርካሪዎች ቢኖሩም ሦስተኛ ወገን መድን ዋስትና ያላቸው ከ 5 መቶ ሺህ አይበልጥም፡፡” በአማራ ክልል የመድን ፈንድ አስተዳድር ኤጀንሲ“በተሽከርካሪ ከተገጩ በኋላ የአካል እንቅስቃሴ አልነበራቸውም፡፡ ለሦስት ቀናት በፈለገ ህይወት ሪፈራል ሆስፒታል የነፃ ህክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ከቆዩ በኋላ አርፈዋል፡፡” ይህ አባታቸውን በመኪና አደጋ ያጡት የወይዘሮ ሙሉጎጃም በላይ ሀሳብ ነው፡፡ነሐሴ 21 2010 ዓ.ም ነበር አባታቸውን በመኪና አደጋ ምክንያት ያጡት፡፡ የአቶ በላይ እጅጉ ሴት ልጅ ሙሉጎጃም አደጋው ከተከሰተ ከስድስት ወራት በኋላ ወደ መድን ፈንድ አስተዳድር ኤጀንሲ በመሄድ እርዳታ ጠየቁ፡፡ የአባታቸውን ህይዎት ባይመልስም ከኤጀንሲው ከ18 ሺህ 9መቶ ብር በላይ ካሳ እንደተሰጣቸው ነግረውናል፡፡ ኤጀንሲው ካሳ እንደሚከፍል ግንዛቤ ያልነበራቸው ወሮ. ሙሉጎጃም አሁን ስለሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ አደጋ ያወቁትን ለሌሎች በማሳወቅ ላይ ይገኛሉ፡፡", "passage_id": "bd085afea70c97b81f8e72a8a6b08e18" }, { "passage": "‹‹ድጋሚ ዕድል የተሰጠው ከፈቃድ ጋር በተያያዘ እንጂ ላስመጪዎች አይደለም›› ገንዘብ ሚኒስቴርከየካቲት 5 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል ከፀደቀው የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2012 ጋር በተያያዘ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) የሰጣቸውን ዕድል አስፈጻሚ የመንግሥት ተቋማት ስለነፈጓቸው፣ ለኪሳራ ሊዳረጉ መሆናቸውን የኢትዮ ተሽከርካሪ አስመጪዎች ባለቤቶች ማኅበር አስታወቀ፡፡ ማኅበሩ እንደሚናገረው የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ ከመፅደቁና በሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት የባንክ ፈቃድ ተሰጥቷቸው ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ የተለያዩ ዕቃዎችን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡ ነጋዴዎች (አስመጪዎች)፣ በቀጣይ ስድስት ወራት ሲያስገቡ ኤሳይስ ታክስ የሚሰላባቸው በነባሩ የኤሳይስ ታክስ አዋጅ ቁጥር 307/2002 ድንጋጌዎች መሠረት መሆኑ አዲስ በፀደቀው አዋጅ ቁጥር 1186/2012 አንቀጽ 43(3) መደንገጉን አስታውሷል፡፡እንደ አስመጪዎቹ ገለጻ አዲሱ አዋጅ በሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት የባንክ ፈቃድ አግኝተው የበርካታ ተሽከርካሪዎችን ግዥ ፈጽመው ለማስገባት በሒደት ላይ እያሉ፣ የዓለም አቀፍ ክስተት የሆነው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ተከሰተ፡፡ የወረርሽኙን መከሰት ተከትሎ የየብስም ሆነ የአየር ትራንስፖርት እንቅስቃሴ ገደብ ስለተጣለበት፣ ከተለያዩ አገሮች የገዟቸውን ተሽከርካሪዎች ከገዙባቸው ከተሞች ወደ ወደብ ማንቀሳቀስ እንኳን አልቻሉም፡፡ የመርከቦችም እንደፈለጉት አለመገኘት ከወደብ ወደ መሀል አገር ለማንቀሳቀስ ካለመቻላቸውም በተጨማሪ፣ ከነባሩ ወደ አዲሱ አዋጅ ለመሸጋገር ተሰጥቶ የነበረው የስድስት ወራት የመሸጋሪያ ጊዜ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት በመቅረታቸው ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ለታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ደብዳቤ መጻፋቸውን ኢትዮ የተሽከርካሪዎች አስመጪ ባለቤቶች ማኅበር ገልጿል፡፡ማኅበሩ ያጋጠመውን ውጥረትና አስቸጋሪ ሁኔታ በመግለጽ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) እና ገንዘብ ሚኒስቴር ሁለት ደብዳቤዎችን አከታትሎ መጻፉንም ጠቁሟል፡፡ ማኅበሩ በጻፈው ደብዳቤ እንደገለጸው ተቋማቱ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተፈጠረበትን አጣብቂኝ ተመልክተው የመሸጋሪያ ጊዜውን እንዲያራዝሙለት መሆኑን አክሏል፡፡አስመጪዎቹ ግምታቸው ከስድስት ቢሊዮን ብር በላይ የሆኑ ተሽከርካሪዎችን የገዙት ቤታቸውንና ሌሎች ንብረቶቻቸውን አስይዘው ከባንክ ተበድረው መሆኑን የጠቆመው ማኅበሩ በየቀኑ እየቆጠረ ያለው የባንክ ወለድ ራሳቸውን አዙሮት እያለ፣ በተገኘው አጋጣሚ ወደ አገር ውስጥ ያስገቧቸውና በአገሪቱ ወደቦች የሚገኙትን ተሽከርካሪዎች፣ የኢትዮጵያ ጉሙሩክ ኮሚሽን ‹‹መቀረፅ ያለባቸው በአዲሱ አዋጅ ነው›› በማለት ለጨረታ እንዳቀረበባቸውም (አዳማ ጉምሩክ) አስረድቷል፡፡ የያዟቸውን ሠራተኞችና የሚያስተዳድሯቸው ቤተሰቦቻቸውን ላለመበተን የመንግሥትን ቀና ምላሽ እየጠበቁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ መንግሥትም ከሌላው ማኅበረሰብ የተለየ ውለታ እንዲያደርግላቸው ሳይሆን የዓለም ክስተት የሆነው ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በፈጠረው ችግርና ከእነሱም አቅም በላይ መሆኑን ተገንዝቦ ለጨረታ የቀረቡትን ተሽከርካሪዎች እንዲያስቆምላቸው፣ ከአዲሱ  አዋጅ በፊት የፈጸሙት ግዥ መሆኑን በመመልከት በነባሩ አዋጅ መክፈል ያለባቸውን ኤክሳይስ ታክስ እንዲከፍሉና ተሽከርካሪዎቻቸውን እንዲረከቡ አቅጣጫ (ትዕዛዝ) እንዲሰጥላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ሰብሳቢ በአቶ ጴጥሮስ ወልደ ሰንበት ፊርማ ወጪ በተደረገ ደብዳቤ፣ የገቢዎች ሚኒስቴር የአስመጪዎችን ችግር መርምሮ ምላሽ እንዲሰጥ ማሳሰቢያ ደርሶት እንደነበር ማኅበሩ አስታውሷል፡፡ቦርዱ ለሚኒስቴሩ በጻፈለት ደብዳቤ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ተመልክቶና መንግሥት ለሌሎች ዘርፎች ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን በማስታወስ ለኢትዮ ተሽከርካሪዎች አስመጪ ባለሀብቶች ማኅበርም ተገቢ ምላሽ በአሥር ቀናት ውስጥ እንዲሰጥና ምላሹን እንዲያሳውቀው ቢያሳስበውም፣ ‹‹አኔን አይመለከተኝም›› ከማለት ባለፈ መፍትሔ ሊሰጣቸው እንዳልቻለም ተናግረዋል፡፡ገቢዎች ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን እንደማይመለከታቸውና የሚመለከተው ገንዘብ ሚኒስቴር መሆኑን በተደጋጋሚ በመግለጻቸው፣ ማኅበሩና አባላቱ ምልልሳቸውን ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር ማድረጋቸውንም አስረድተዋል፡፡ማኅበሩ ለገንዘብ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ እንደገለጸው በኮቪድ-19 ምክንያት በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ እንደ ልብ መንቀሳቀስ ባለመቻሉና የአየር ትራንስፖርት በመታገዱ፣ የገዟቸውን ተሽከርካሪዎች ከከተሞች ወደ ወደብ ማንቀሳቀስ ባለመቻላቸው  ወደብ ላይ የደረሱትንም መርከቦች በወቅቱ ባለመገኘታቸው መጫን ባለመቻላቸው፣ መዳረሻ ወደብ (ጂቡቲ ወደብ) ላይ የደረሱትንም ማምጣት ባለመቻላቸው በአገሪቱ በተፈጠረው የኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ምክንያት ገበያቸው በመቀዛቀዙ የጉምሩክን ቀረጥ በወቅቱ ሊከፍሉ ባለመቻላቸው፣ ተሽከርካሪዎቹን በወቅቱ አገር ውስጥ ማስገባት አለመቻላውን አስረድተዋል፡፡ በመሆኑም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ያመጣው ቀውስ መሆኑን መንግሥትም ስለሚረዳ፣ ሚኒስቴሩ ተረድቷቸው አገር ውስጥ የገቡ፣ በተለያዩ ወደቦች የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን በነባሩ አዋጅ የሚተመንባቸውን ኤክሳይስ ታክስ እንዲከፍሉና ከፍተኛ የወደብ ኪራይ (ዲመሬጅ) እየቆጠረባቸው የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን እንዲያስገቡ መጠየቃቸውን ሰነዶች ያሳረዳሉ፡፡ገንዘብ ሚኒስቴር በሕግ ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ መነሻ በኩል በሰጣቸው አጭር ምላሽ አዲሱ አዋጅ ከፀናበት ቀን በፊት በተገኘ የባንክ ፈቃድ ግዥ የፈጸሙ በስድስት ወራት የመሸጋገሪያ ጊዜ ውስጥ ሲያስገቡ በነባሩ ሕግ እንደሚቀረጡ ተናግሮ፣ ከመሸጋገሪያ ጊዜው ውጭ ለማራዘም ሚኒስቴሩ በሕግ ሥልጣን እንዳልተሰጠው በመግለጽ አቤቱታቸውን ሳይቀበለው መቅረቱንም ተናግረዋል፡፡ ሁለም ዜጋ የሚገዛበትን ሕግ የሚያወጣው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰጣቸውን ዕድል አስፈጻሚው በመንፈጉ እነሱን ለኪሳራ፣ ሠራተኞቻቸውን ለሥራ አጥነትና ቤተሰቦቻቸውን ለጎዳና ሊዳረጉ ጫፍ ላይ በመድረሳቸው መንግሥትና የሚመለከተው አካል እንዲደርስላቸው ተማፅነዋል፡፡የኢትዮ ተሽከርካሪዎች አስመጪ ባለቤቶች ማኅበር ያቀረበውን አቤቱታ በሚመለከት ሪፖርተር ገንዘብ ሚኒስቴርን ጠይቆ አጭር ምላሽ ተሰጥቶታል፡፡ የሚኒስቴሩ ሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ሰመሪታ ሰዋሰው እንደገለጹት አስመጪዎቹ በተሰጣቸው ጊዜ ማስገባት ነበረባቸው፡፡ ፓርላማው ሁለተኛ ዕድል የሰጠው ላስመጪዎች ሳይሆን ከላይሰንስ (ፈቃድ) ጋር ለተያያዙ ጉዳዮች እንጂ ላስመጪዎች አይደለም፡፡ ‹‹ተሽከርካሪ አስመጪዎች ሌሎች አስመጪዎች እንደሚያደርጉት ከፍለው ማስገባት አለባቸው፤›› ብለዋል፡፡  ", "passage_id": "05c9a48fce6ddebdf505491af5193e7b" }, { "passage": "ከዛሬ አርብ ሚያዚያ 30/2012 ጀምሮ የሚኒ ባስ ታክሲ ተጠቃሚዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችን ማድረግ እንደሚገደዱ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ እንዳስታወቀው በአዲስ አበባ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችን የማያደርጉ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎች ላይ ከማስተማር እስክ ሕጋዊ እርምጃ የሚደርስ ቅጣትን እንደሚጥል አስጠንቅቋል፡፡የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመግታት የትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ጭምብል እንዲጠቀሙ ይደረጋል ያሉት የቢሮ ኃላፊው ስጦታው አካለ፤ ይሁንና በቸልተኝነትም ይሁን በሌላ መልኩ ጭምብል ያላደረጉ ተሳፋሪዎች በመጀመሪያ ትምህርት ይሰጣቸዋል ሲሉም ለኢዜአ አስታውቀዋል፡፡እንደ ኃላፊውም ገለጻ ተጠቃሚዎች ተሽከርካሪ ውስጥ ሲገቡ ብቻ ሳይሆን፤ ሰልፍ ላይም ሆነው ጭምብል እንዲያደርጉ ይገደዳሉ ይህንን በማያደርጉ ተጠቃሚዎች ላይ ግን የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ መሠረት እንደሚዳኙና የትራንስፖርት አገልግሎትም ማግኘት እንደማይችሉ ኃላፊው አስታውቀዋል።በተጨማሪም የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር የሚወጡ መመሪያዎችን በትክክል በመተግበር ጥንቃቄ ማድረግ ወሳኝነት እንዳለው ያሳሰቡት ኃላፊው “በከተማዋ የሚስተዋለው የኅብረተሰቡ ቸልተኝነት ከበሽታው ስርጭት ጋር የሚቃረን ሆኖ አግኝተነዋል” ስለሆነም መንግሥት የወረርሽኙን ስርጭት በመቆጣጠር አገርንና ሕዝብን ለማዳን የሚያደርገው ጥረት ጥቅሙ ለራስ መሆኑን ህብረተሰቡ መረዳት ይገባል ብለዋል።የፐብሊክ ሰርቪስ ሠራተኞች ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ከዕሮብ ጀምሮ ተሳፋሪዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችን በአስገዳጅ ሁኔታ እንዲጠቀሙ ማድረግ መጀመሩም የሚታወስ ነው።", "passage_id": "205cc0ff2086f3a066c440021aa3db13" }, { "passage": "ኮሮናቫይረስ፡ ኢንሹራንስና ቤት ለኮሮናቫይረስ ጤና አገልግሎት ሰጪዎች\\nዶክተር ሊያ ታደሰ\n\nበብዙ አገራት እየሆነ እንዳለው በኢትዮጵያም የጤና ባለሙያዎችም ሆነ በቀጥታ ከህሙማኑ ጋር የሚሰሩ ሰዎች ምርመራ ማድረግ፣ በአምቡላንስ መውሰድ፣ ለህመምተኞቹ ድጋፍና ምቾትን እንዲሁም መድኃኒትን ከማዘዝ ጀምሮ ለብዙዎች ስጋት የሆነውን ቫይረስ በቀጥታ እየተጋፈጡት ይገኛሉ።\n\nበዚህም ምክንያት በርካታ የጤና ባለሙያዎችም ሆነ ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ህይወታቸው አደጋ ውስጥ ገብቷል። \n\nከሰሞኑም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የሚሰሩ ድጋፍ ሰጪ አካላትም ሆነ የጤና ባለሙያዎች በኢንሹራንስ እንዲሸፈኑ ውሳኔ ላይ ደርሷል።\n\nከኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ ህይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው ወረርሽኙን ለመቆጣጠር እየሰሩ ያሉ ባለሙያዎኞች ለስድስት ወር ያህል የኢንሹራንስ ሽፋን ለመስጠት ስምምነት ላይ መደረሱን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል።\n\nኢንሹራንሱ ዶክተሮችና ነርሶችን ብቻ ሳይሆን በፅዳት ላይ የተሰማሩ፣ የአምቡላንስ አሽከርካሪዎች ወይም ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች ጋር በቀጥታ የሚሰሩ ሠራተኞችን በሙሉ ይመለከታል።\n\n\"ቫይረሱ ለጤና ባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን በሌላ ሥራ ለተሰማሩት እንደ ፅዳት ወይም የአምቡላንስ ሾፌሮች ስጋት ሆኗል። ለበሽታውም ተጋላጭ ናቸው። በዚህ ምክንያት በሽታው ቢይዛቸውና ህይወታቸው አደጋ ላይ ቢወድቅ ምን መሆን አለበት? የሚለውን ታሳቢ በማድግ ነው የኢንሹራንስ ስፋን እንዲያገኙ የተወሰነው\" ብለዋል ሚኒስትሯ ለቢቢሲ። \n\nይህንን የኢንሹራንስ ሽፋን የሚሰጠው የኢትዮጵያ መድን ድርጅት እንደሆነና አገልግሎቱን ያቀረበው በነፃ እንደሆነና ሃሳቡም ከእራሱ ከድርጅቱ የመጣ መሆኑን ሚኒስትሯ ጠቅሰዋል። \n\nበተጨማሪም ሌሎች ለመደገፍ ፍላጎት ያላቸው የኢንሹራንስ አገልግሎት ሰጪዎች ጋርም ውይይት መጀመሩን ያመላከቱት ሚኒስትሯ መንግሥትም ሰፋ ባለ መንገድ የኢንሹራንስ ሽፋን የሚሰጥበትን መንገድ እየቀየሰ መሆኑን ተናግረዋል። \n\nከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎችም ሆነ ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ቁጥር በየጊዜው የሚለዋወጥና እየጨመረ የሚሄድ ከመሆኑ አንፃር የኢንሹራንሱ ሽፋንም ሆነ የመኖሪያ ቤት የሚያገኙ ሰዎችን ቁጥር በትክክል መናገር ከባድ እንደሆነም ገልፀዋል።\n\nዶክትር ሊያ እንደሚሉት በአገሪቱ ውስጥ የቫይረሱን ወረርሽኝ ለመቆጣጠር በሺህዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞች ተሰማርተዋል፤ በዚህ ዓመት እንኳን አዲስ የተቀጠሩ 3800 ባለሙያዎች አሉ። ኢንሹራንስ ሽፋኑም እነዚህን ጨምሮ ለወደፊቱ የሚቀጠሩትንም የሚያካትት ይሆናል። \n\nከኢንሹራንስም በተጨማሪ የኮቪድ-19 ህክምና በሚሰጥባቸው ማዕከላት ቀጥታ ፈጣን ምላሽ እየሰጡ ያሉ የጤና ባለሙያዎች ወደየቤታቸው መመላለሱ ስጋት በመፍጠሩ ከዚህ ስጋት ነፃ ሆነው የሚሰሩበትም ሁኔታ ለማመቻቸት ቤቶች እንዲሰጣቸው መወሰኑን አመልክተዋለወ። \n\nአንዳንድ ሆስፒታሎች በተለይም ማስተማሪያ ያላቸው ተቋማት ተማሪዎች ይጠቀሙባቸው የነበሩ ዶርሚተሪዎች (የማደሪያ ክፍሎች) ተማሪዎቹ በአሁኑ ወቅት ስለሌሉ ለዚህ አገልግሎት እያዋሉ መሆኑን ሚኒስትሯ ተናግረዋል።\n\nከዚህም በተጨማሪም በቅርቡ ኖህ ሪል ስቴት የተባለው የግል ድርጅት የሰጠውን አፓርትመንት (የጋራ መኖሪያ ቤት) አልጋዎችና ቁሳቁሶች ተሟልተውለት ለጤና ባለሙያዎቹ አገልግሎት እንደሚውል ሚኒስትሯ ለቢቢሲ ገልፀዋል።\n\nምንም እንኳን ኢንሹራንሱ ለሁሉም ሰራተኞች ቢሆንም የቤት አሰጣጡ ግን እንደ ጤና ባለሙያዎቹ የአኗኗር ሁኔታ እንደሚወሰን ሚኒስትሯ አስረድተዋል። \n\nአሁን ባለው መሰረት ከስድስት መቶ በላይ ለሆኑ ባለሙያዎች ቤት እንዲሰጣቸው ተለይተዋል፤ ይህም በአዲስ አበባ ሲሆን በየክልሉ ደግሞ ዩኒቨርስቲዎችም እየተዘጋጁ ነው። \n\nምርመራና የመለየት...", "passage_id": "2a552d54fd43bcb223aa18e4e2064275" }, { "passage": "የድንበር አቋራጭ ከባድ የመኪና አሽከርካሪዎች እና ረዳቶች ለወረርሽኙ ካላቸው ተጋላጭነት አንጻር በወደቡ ገቢ ጭነት ሲያራግፉም ሆነ ወጪ ጭነት ሲጭኑ በሚኖረው ሂደት የዘመቻ ስራው በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተከናወነ እንደሚገኝ የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ገለፀ፡፡ከአሁን በፊትም በወደቡ የሰው ንክኪ በሚበዛባቸው አካባቢዎችና ገቢ ጭነት ይዘው የሚገቡ ተሽከርካሪዎችን የጸረ ተህዋስያን ኬሚካል ርጭት የማካሄድ፣ ማንኛውም አሽከርካሪና እና ረዳት ወደ ወደቡ ሲገባ እና ጭኖ ሲወጣ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ማስክ እና የሙቀት ልኬት ማድረግ፡ አስገዳጅ ሆኖ እየተሰራበት ይገኛል፡፡በዚህ መሰረትም ዛሬ ግንቦት 07ቀን 2012 ዓ/ም ከኢትዬጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት ጋር በመተባበር በአሽከርካሪዎችና ረዳቶች ላይ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ የተጀመረ መሆኑን ከፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን መ/ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።", "passage_id": "0d07f4d5ba0a47a9272e4ea04ffaed97" } ]
ee07b1a5d2012640481cad382aae63b8
4aae59a0d3f6cbb46547985bf8b6a26a
በተመድ ሲሰሩ የነበሩና በጡረታ የተገለሉ ሴት ኢትዮጵያውያን በህዳሴው ግድብ እየሰሩ ለሚገኙ ሴቶች የ600 ሺ ብር ስጦታ አበረከቱ
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡- ሀገራቸውን ወክለው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በተለያየ ደረጃ ሲያገለግሉ የነበሩና በጡረታ የተገለሉ ሴት ኢትዮጵያውያን በህዳሴው ግድብ ላይ እየሰሩ ለሚገኙ ሴቶች የ600 ሺህ ብር ሥጦታ ማበርከታቸውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ብሔራዊ ምክር ቤት አስተባባሪ ፅህፈት ቤት አስታወቀ።በሥጦታ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የፅሕፈት ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አረጋዊ በርሔ እንደገለፁት፤ ሀገራቸውን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በተለያየ የሥራ መስክ ሲያገለግሉ የቆዩ እና አሁን ላይ በጡረታ ወደ ሀገራቸው የተመለሱ እናቶች በታላቁ በህዳሴ ግድብ ላይ በጥበቃ ለሚገኙ ሴት የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለሳሊኒ ፕሮጀክት ሰራተኞች እያደረጉት ላለው ታሪካዊ ስራ ያላቸውን ፍቅር ‹‹የእናቶች መቀነት ለግድባችን ልማት›› በሚል ሀሳብ ስጦታ አበርክተዋል።እንደ ዶክተር አረጋዊ ገለፃ፤ በግድቡ ላይና በግድቡ ዙሪያ በበርካታ አካባቢያዊ ተፈጥሯዊና ማህበራዊ ተግዳሮቶች ውስጥ ሆነው የትውልድ ሃውልት በማቆም ሥራ ላይ እየተሳተፉ ላሉ 450 ወጣት ሴቶችና በግድቡ ግንባታ ያለውን የሰላም እና የፀጥታ ሥራ ለሚሰሩ ለእያንዳንዳቸው የአንድ ሺ ብር ቦንድ፣ ግድቡን ለሚገነባው ተቋራጭ 50 ሺብር፣ ለውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት 50ሺ ብር፣ በድምሩ 600 ሺ ብር ቦንድ በመግዛት ትውልድ የማይረሳው ትልቅ አሻራ አስቀምጠዋል።በሌላ በኩል በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች መሥሪያ ቤት ለ27 ዓመት አገልግለው በጡረታ የተመለሱት ወይዘሮ ገነት ገብረ ክርስቶስ እንደገለፁት፤ ከራሳቸው ጡረታ ደመወዝና ልጆቻቸውን ጠይቀው በጭስና በእንጨት ሸክም ለሚደክሙ የኢትዮጵያ እናቶችን ችግር እንዲቀርፍ ለሚገነባው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሰራተኞች የቦንድ ሥጦታ ለማበርከት እንደተነሳሱ ተናግረዋል።ግድቡ የሁላችን በመሆኑ የእያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት እንዳለበት ጭምር ለማሳየት ተርፏቸው ሳይሆን ከሚያገኙት ትንሽ የጡረታ ደሞዛቸው ቀንሰው ማበርከታቸው የዜግነት ግዴታ ከመሆኑም ባሻገር ለሀገር ያላቸውን ፍቅር ለመግለፅ እንደሆነ ወይዘሮ ገነት ገልፀዋል።እናቶች ሥጦታውን ያበረከቱት የመከላከያ ሰራዊት ኢንዶክትሪኔሽን ኃላፊ ሜጀር ጄኔራል መሃመድ ተሰማ፣ የፌደራል ፖሊስ ተወካይ ኢንስፔክተር ፀደይ አቤኔዘር፣ የህዳሴው ግድብ ምክትል ስራ አስኪጅ አቶ በላቸው፤ የሳሊኒ ኮንስትራክሽን ተወካይ አቶ ታምሩ እና የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍሬ ህይወት በተገኙበት በሴቶች፣ ህፃናት ወጣቶች ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ሚኒስትሯ በተገኙበት ቦንዱን አስረክበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38083
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት በአዲስ አበባ ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች የዊልቸር ድጋፍ አበረከተ፡፡ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ዛሬ ከአዲስ አበባ ከተማ ለተውጣጡ 72 አካል ጉዳተኞች የመንቀሳቀሻ ዊልቸሮችን በስጦታ አበርክተዋል፡፡ስጦታ ባበረከቱበት ወቅት እንዳሉትም ይህ ስራ በቀጣይነት በአዲስ አበባ እና በክልሎች ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡የዊልቸር ስጦታዎቹ የተገኙት ሞቢሊቲ ወርል ዋይድ እና የአብ ሜዲካል ከተባሉ በጎ አድራጊ ድርጅቶች መሆኑ ታውቋል፡፡ዊልቸሮቹ በተለይም በተለያየ የግል ስራ ላይ በመሰማራት ተንቀሳቅሰው ገቢ ለማግኘት ለሚጥሩ የአካል ጉዳተኞች ተስማሚ ሆኖ የተሰሩ በመሆናቸው ለስራ ፈጠራ ከፍተኛ እገዛ ይኖራቸዋል መባሉን ከፅህፈት ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።", "passage_id": "765001b80a627ccf04bba3b0177ac379" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በመንግስት ትምህርት ቤት ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች ሞዲስ እና ሌሎች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በነጻ ለማቅረብ የከተማ አስተዳደሩ ከተለያዩ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል።በዚሁ መሰረት የፊታችን ታህሳስ 28 ቀን 2012ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር መዘጋጀቱን አስተባባሪዎቹ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።በመርሃ ግብሩ 700 ሺህ ሞዴስ እና 200 ሺሕ የሴቶች ፓንት ለማሰባሰብ እቅድ መያዙ የተገለጸ ሲሆን በመርሃ ግብሩም ከ20 ሺህ በላይ በጎ ፍቃደኞች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሏል።በዚህ ዕለትም በአሜሪካው የዜና አውታር ሲ.ኤን.ኤን የአመቱ ጀግና ተብላ የተሸለመቺው ፍሬወይኒ መብረሃቶም የክብር አቀባበል እንደሚደረግላት ተገልጿል።ማንኛውን የከተማዋ ነዋሪዎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የሚችሉትን ሞዴስ ፣የሴቶች ፓንት እና ሌሎች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በመያዝ መግባት እንደሚችሉ አዘጋጆቹ አመልክተዋል።ማንኛዉም ሰዎች የሚሉችን ሞዴስ እና የሴቶች ፓንት እንደመግቢያ መያዝ በፕሮግራሙ መታደም እንደሚችሉ ከከተማው ፕሬስ ሴክሬተሪያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡በአዲስ አበባ ከተማ በትምህርት ላይ ከሚገኙ ጠቅላላ ተማሪዎች ከ50 በመቶ በላዩ ሴቶች ሲሆኑ በየወሩ ከሁለት እስከ ሶስት ቀናት ከወር አበባ ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ከትምህርት ቤት እንደሚቀሩ ጥናት ማመልከቱ ተጠቁሟል፡፡", "passage_id": "660ccb8d223f07499ad223ab8d91244e" }, { "passage": "በባህርዳር ከተማ ቀበሌ አንድ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተወልዳ ያደገችው ብርቱካን ጀምበሩ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን ጨርሳ ወደ ሁለተኛ ደረጃ ስትሻገር ከትምህርቷ ይልቅ የሚያሳስባት የቤተሰቧ አቅም ማነስ እና የፅዳት ስራ እየሰራች የምታሳድጋት እናቷን ማሳረፍ የምትችልበት መንገድ ነበር። በወቅቱ 18 አመት እንኳን ያልሞላት ብርቱካን ወደ አረብ ሀገር ሄዳ እየሰራች ለእናቷ ገንዘብ መላክ እንደምትችል ስትሰማ ለአፍታ አላመነታችም። እናቷ ተበድራ ባመጣችው ገንዘብ በልጅነት እድሜዋ ወደ ሳውዲ አመራች።ብርቱካን ካሰሪዋ ጋር መስማማት ባለመቻልዋ በአንድ አመት ግዜ ውስጥ ወደ ሀገሯ ስትመለስ ባል በማግባት ኑሮን ለማሸነፍ ሞከረች \"ግን እሱም አልተሳካም\" ትላለች ብርቱካን። ልክ እንደ ብርቱካን በአፍላ እድሜያቸው ራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠው፣ የቤተሰባቸውን የኑሮ ሁኔታ ለመደጎም ወደ አረብ ሀገራት የሚፈልሱ ሴት ህፃናት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱንና፣ ይሄም ትምህርታቸውን ለሚያቋርጡ ሴት ተማሪዎች ምክንያት መሆኑን የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው መምህራንና የትምህርት ቢሮ ሀላፊዎችም ያስረዳሉ።በአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት ዶክተር ይልቃል ከፍያለ እንደገለፁልን በአሁኑ ሰዓት በክልሉ እንደ ያለ እድሜ ጋብቻ ከመሳሰሉት ባህላዊ ተፅእኖዎች በበለጠ በቤተሰባቸው የኑሮ አቅም ምክንያት የሴቶች ህፃናት ፍልሰት ለትምህርት ማቋረጣቸው ዋነና ምክንያት እንደሆነ ያስረዳሉ። አብዛኞቹ ሴት ህፃናት ትምህርታቸውን አቋርጤው ከሀገራቸው የሚወጡት በህገ-ወጥ መንገድ፣ በደላላ አማካኝነት ነው። ለጉዞ የሚሆን ገንዘብም ስለማይኖራቸው ነገ ልጆቹ ሰርተው ይከፍላሉ በማለት ቤተሰቦቻቸው ንብረታቸውን ሸጠው አሊያም ተበድረው ልጆቹን በብዛት ወደ አረብ ሀገራት ይልኳቸዋል። በአማራ ክልል 26 ከመቶ የሚሆነው ህዝብ ከድህነት ወለል በታች እንደሚኖር የሚያስረዱት አቶ ይልቃል፣ ሀገሪቱ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን የምትፈታበት አቅም ላይ ባለምድረሷ በአቋራጭ ገንዘብ አግኝቶ ቤተሰብን ለማገዝ የሚደረግ ጥረት ለህገወጥ ፍልሰት ይዳርጋል ይላሉ።በሀገርቱ ውስጥ እየተባባሰ የሄደው የተመረቁ ተማሪዎች ስራ አጥነትም፣ ሴቶች በትምህርታቸው እንዳይገፉ እንደሚያደርጋቸውም ይገለፃል። በጉዳዩ ላይ ያናገርነውና በባህርዳር ከተማ ኤስ ኦ ኤስ ትምህርት ቤት መምህር የሆነው ደጉ ምናለ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቁጥሩ እየጨመረ የመጣው የሴት ተማሪዎች ህገወጥ ፍልሰት ከምጣኔ ሀብት ዝቅተኛ መሆን በተጨማሪ ተምረን የትም አንደርስም ከሚል አስተሳሰብ የመጣ መሆኑን ያስረዳል።በአሁኑ ሰዓት ከእናቷ ጋር ሆና ሽሩባ በመስራት የምትደዳደረው ብርቱካን በልጅነት የሞከረችው የመጀመሪያው የሳውዲ ጉዞዋ ባይሳካላትም ቤተሰቧ ካለበት የኢኮኖሚ ችግር አንፃር፣ አሁንም ወደ አረብ ሀገር ሄዳ ገንዘብ ማግኘት እመርጣለሁ ትላለች።ከህገወጥ ፍልሰት በተጨማሪ ታዳጊ ህጻናት በጾታቸው ምክንያት ሲደርስባቸው የኖረው የሀይል ጥቃት፣ እንያለዕድሜ ጋብቻና የመሳሰሉት ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በተለይ በገጠሪቱ የኢትዮጵያ ክፍሎች አሁንም እንደቀጠሉ ናቸው። ሰሜን ሸዋ መረሀቤቴ ውስጥ፣ ለሚ ተብላ በምትጠራ መንደር ተወልዳ ያደገችው ሀና ደቹ ገና በለጋ እድሜዋ የአራተና ክፍል ተማሪ እያለች ይህን አይነቱን ያለእድሜ ጋብቻ ለማምለጥ አዲስ አበባ የምትኖር አክስቷን ለምና በመምጣቷ ዛሬ 9ኛ ክፍል ደርሳለች። ለሚ ቀርታ ትማር የነበረችው ታናሽ እህቷ ግን በ 15 አመቷ ከ 8ኛ ክፍል አቋርጣ በቅርቡ ልታገባ ቤተሰቦቿ እየተዘጋጁ መሆናቸውን ሀና በሀዘን ትናገራለች። በቤንሻንጉል ጉምዝ፣ በድባቅና ዳንጉር ወረዳዎች ከ25 አመታት በላይ በትምህርት ባለሙያነት ያገለገሉትና በአሁኑ ሰአት በባህርዳር ከተማ አስተዳደር መሸንቲ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ እድሜውገፍቶ በቤንሻንጉልና በአማራ ክልል ያሉትን ችግሮች አነፃፅረው እንዲህ ያስረዳሉ። አቶ ሙሉጌታ እንደገለፁልን በቤንሻንጉል ጉምዝ እሳቸው መምህር ሆነው ባገለገሉባቸው አካባቢዎች የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ከ 15 ወደ 50 ከፍ እንዲሉ ቢደረግም፣ የሁለተኛ ደረጃ ተቋማት ግን ሶስት ብቻ በመሆናቸውና፣ በቅርብ ርቀትም ላይ ስለማይገኙ ሴት ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ይገደዳሉ። በቤንሻንጉል ጉምዝ ደንጉር ወረዳ በሴት ተማሪዎች ላይ የሚደርሰውን ፆታዊ ጥቃት ለመቀነስና በርቀት ምክንያት ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ ለመገዝ የአዳሪ ትምህርት ቤቶች ለማቋቋም ጥረት እንደተድረገ አቶ ሙሉጌታ ይገልፃሉ። ነገር ግን ያለው ችግር ህብረተሰቡ ለሴቶች ትምህርት ካለው ግንዛቤ ማነስ ጋር ተደምሮ ችግሩን ሙሉ ለሙሉ መፍታት አልተቻለም። በአካባቢያቸው የትምህርት ተቋም ባለመኖሩ ከከተማቸው እርቀው ለመኖር የሚገደዱ ሴት ተማሪዎች ከሚደርስባቸው ፆታዊ ትንኮሳ በተጨማሪ በትንሽ ነገር በመታለል ያላሰቡት ኑሮ ውስጥ እንደሚገቡም በባህርዳር ኤስ ኦ ኤስ አስተማሪ የሆነው ደጉ ያስረዳል። ደጉ ሌላው የሚያሳስበው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፓለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ተማሪዎች ላይ የሚደርሲ ችግሮች ናቸው። እነዚህ ችግሮች ወላጆች በተለይ በተለያዩ ክልሎች ያሉ ዩንቨርስቲዎች ውስጥ የሚመደቡ ሴት ልጆቻቸውን ለመላክ እንዲፈሩ እንደሚያደርጋቸው፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህም በዚህም ምክንያት ትምህርታቸውን የሚያቋርጡ ሴት ተማሪዎች እየተበራከቱ መምጣታቸውን ደጉ ይገልፃል።በኦሮሚያ ክልል፣ በነቀምት ከተማ የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተግዳሮት ሁኔታ ለማወቅ ያናገርናቸው የነቀምቴ ከተማ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አሸናፊ ከበደ ሁንዴሳ በበኩላቸው በከተማው ያለ እድሜ ጋብቻና ሌሎች ባህላዊ ተፅእኖዎች በአንፃራዊነት ዝቅተኛ መሆናቸውንና ትምህርታቸውን የሚያቋርጡ ሴት ተማሪዎች ቁጥር 1.3 ከመቶ ብቻ መሆኑን ነግረውናል። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአለም ዙሪያ በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው በሴት ህፃናት ላይ የሚደርሱ ፆታዊ ጥቃቶች፣ ያለ እድሜ ጋብቻና የቤት ውስጥ ስራ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመሩ መሆኑን የተለያዩ መረጃዎች አመልክተዋል። ለወትሮው በሴት ተማሪዎች ዙሪያ የሚደርሱ ችግሮችን በቅርበት የሚከታተሉትና የመረጃ ምንጭ ሆነው የሚያገለግሉት ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው ግን በአሁኑ ሰዓት ሴት ህፃናት ላይ እየደረሱ ያሉ ተግዳሮቶች ለመከታታል የበለጠ አዳጋች እንደሆነ የትምህርት ባለሙያዎቹ አስረድተዋል።\n ", "passage_id": "a3e035c9e54efe2ac9e1323a73ff0077" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ህዳር 9 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አመራሮችና ሰራተኞች በህግ የማስከበር ዘመቻ ላይ ለሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ደም ለገሱ።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ተገኝተው ደም ለግሰዋል።ባንኩ በመላው ሀገሪቱ ከ 63 ሺህ በላይ ሰራተኞች ሲኖሩት በዛሬው እለትም ሁሉም ሰራተኞች ደም በመለገስ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡በደም ልገሳው ላይ የተሳተፉ ሰራተኞች የህወሓት ቡድን የሀገር አለኝታ በሆነው በመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈፀመውን ጥቃት ሲሰሙ ከፍተኛ ሀዘን እንደሰማቸው ገልጸዋል።ጽንፈኛውና ዘራፊው የህወሓት ቡድን በሀገር አለኝታ በሆነው በመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈፀመውን ጥቃት ተከትሎም ደም እየለገሱ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።ሰራተኞቹ አያይዘውም መከላከያ ሰራዊትን መደገፍ ከሁሉ ነገር መቅደም ይገባልም ነው ያሉት፡፡አያይዘውም ሀገርን ለማዳን በዱር በገደሉ እየተዋደቀ ለሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት ደም ከመለገስ ባለፈ በገንዘብና በሌሎች ድጋፍ በሚያስፈልጉ ጉዳዮች አስፈላጊውን ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።በፈትያ አብደላ", "passage_id": "54812c53b2358e7fcff9608ba90574c2" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ ኅዳር 05/2013 ዓ.ም (አብመድ) መንግስት እየወሰደ ባለው ህግ የማስከበር ስራ ሴቶች የቀደምት እናቶችን ተጋድሎ በማስቀጠል የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ የአማራ ሴቶች ማህበር ሊቀመንበር ወይዘሮ ትብለጥ መንገሻ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ከአብመድ ጋር ቆይታ ያደረጉት የአማራ ሴቶች ማሕበር ሊቀመንበር ወይዘሮ ትብለጥ መንገሻ ዘራፊውና ከሃዲው የህወሓት ቡድን ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም በጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ክህደት ከመፈጸሙ በፊትም በሃገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በንጹኅን ዜጎች ላይ ጥቃት ሲፈፅም መቆቱን አስታውሰዋል፡፡የህወሃት ቡድን በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በመተከል ዞን ፣በኦሮሚያ ክልል ወለጋ፣ በጉራፈርዳ እና በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች በነበረው ጥቃት የችግሩገፈት ቀማሽ ሴቶች፣ ህጻናትና አካል ጉዳተኞች መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡አሁንም ጉዳት እየደረሰባቸውና ለችግር እየተጋለጡ የሚገኙ በተለይ ህጻናት፣ ሴቶች፣ አረጋውያንና አካል ጉዳተኞች በመሆናቸው የትግራይም ሆነ የአማራ ክልል ሴቶች በህብረት ሊሰሩ እንደሚገባ ወይዘሮ ትብለጥ አሳስበዋል፡፡ከሀዲው የትህነግ ቡድን ሃገር የማፍረስና ህዝቦችን የመነጣጠል ተልዕኮ አንግቦ እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም ይህ ህልሙ እንዳይሳካ ለማድረግ ሴቶች የቀደምት እናቶችን ተጋድሎ በማስቀጠል የህወሃትን ቡድን ለመንግስት አጋልጦ በመስጠት፣ ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ደም በመለገስ፣ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ አጋርነታቸውን ሊያረጋግጡ ይገባል ብለዋል ሊቀመንበሯ፡፡", "passage_id": "573d67a371e559a7d1e51e706a731285" } ]
f739bc758089e9153e6b5705d1533b9a
56896bdd81ecea429d72c618b908ed3d
በመተከል ዞን ለሕዝብ ጥቅም የሚሠራ አመራርና አደረጃጀት እንዲመቻች ተጠየቀ
አሶሳ(ኢዜአ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን በየጊዜው የሚከሰተው ግጭት በዘላቂነት ለመፍታት ለሕዝብ ጥቅም የሚሠራ አደረጃጀት፣ አመራር እና አሰራር እንዲመቻች ተጠየቀ። በዞኑ የጸጥታ ችግር ላይ የክልሉ ነዋሪዎች በአሶሳ ከተማ ሲያካሂዱ የቆዩት የማህበረሰብ ምክክር ከትናንት በስቲያ ማምሻውን የተጠናቀቀ ሲሆን፤ ነዋሪዎቹ በአስር ቡድኖች ተከፋፍለው ባደረጉት ውይይት በዞኑ ዋነኛ ችግሮች እና መፍትሔ ያሏቸውን ሀሳቦች አንስተዋል።ከቡድኖቹ አስተባባሪዎች መካከል አቶ ሞላ አስማረ ለዞኑ የጸጥታ ችግር መባባስ በየደረጃው የሚገኘው አብዛኛው አመራር አድሎአዊ አሠራር መከተሉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ማንሳታቸውን አመልክተዋል። የዞኑ አመራር ከሕዝብ ጥቅም ይልቅ የራሱን ሲያስቀድም እንደነበር ተወያዮቹ አንስተዋል ብለዋል።ችግሮች ሲፈጠሩ አመራሩ ኃላፊነት ወስዶ መፍትሔ ከመስጠት ይልቅ ተጠያቂነትን ይሸሹ እንደነበር ያስታወሱት አስተባባሪው፤ በየደረጃው ባሉ አመራሮች በችግሩ ላይ በሚደረጉ ውይይቶች የሃሰት ሪፖርት ይቀርቡ እንደነበረ ጠቁመዋል።የዞኑ የጸጥታ ችግር በአብዛኛው በመገናኛ ብዙሃን ተገቢውን ሽፋን አላገኘም ያሉት አቶ ሞላ፤ በማህበራዊ ትስስር ገጾች የሚቀርበው የፈጠራ ወሬም ችግሩን እንዳባባሰው አስረድተዋል። የሕግ የበላይነትን በማስከበር በዞኑ ፖሊስ፣ ፍርድ ቤት እና ሌሎችም ፍትህ አስከባሪ ተቋማት ችግሮች እንደሚታዩባቸው አንስተዋል።ሌላው የቡድኑ አስተባባሪ አቶ በሱፈቃድ አስረስ በበኩላቸው፣ የመሬት ወረራ ለዞኑ ግጭት ሌላው ተጠቃሽ ምክንያት እንደሆነ አመልክተው፤ በአጠቃላይ ሕግን በማስከበር ደረጃ የሚታየው ክፍተት የአካባቢው ጸጥታ ችግር በፍጥነት እንዳይፈታ እንዳደረገው ተናግረዋል። በዞኑ ብልሹ አሰራርን የሚታገል፣ ለሕዝብ ጥቅም የሚሰራ አመራር እና አደረጃጀት መፍጠር ዋነኛው እንደሆነ ነዋሪዎቹ ለችግሮቹ መፍትሔነት ሀሳብ ማቅረባቸውንጠቅሰዋል። የህብረተሰቡን ፍላጎት መሠረት ያደረገ መሠረተ ልማት ማስፋፋት፣ የመንግስት አደረጃጀት እና መዋቅርን በጎጠኛ አስተሳሰብ ከሚያራምዱ አመራሮች ማጽዳት እንደሚገባም አመላክተዋል።በዞኑ በተለይም የመሬት አስተዳደር ሕግን በሚገባ የሚተገበርና መልካም ስነ-ምግባር ያለው እና ሕገ-መንግሥቱን የሚያስከብር አመራር መፍጠር ሌላው የውይይቱ ተሳታፊዎች ያስቀመጡት መፍትሔ እንደሆኑ ያመለከቱት ደግሞ ሌላው አስተባባሪ አቶ ሻምበል ተገኝ ናቸው።አቶ ሻምበል፣ በዞኑ አስተዳደር ከሕዝብ ስብጥር እና ቁጥር ጋር የተመጣጠነ ውክልና ያለው አሠራር ሊኖር እንደሚገባ ነዋሪዎቹ ሀሳብ ማቅረባቸውንም ጠቁመዋል። በፍትህ ተቋማትም ሕጉን በአግባቡ የሚተገብር ባለሙያ እና አመራር መመደብ እንደሚያስፈልግም ተጠቅሷል።ሃዋርያ ክፍሌ ይልማ በበኩላቸው፣ እያንዳንዱ የዞኑ ነዋሪ ለጸጥታ አካላት ትክክለኛ መረጃ በመስጠት አብሮ መስራት እንዳለበት ጠቁመው ፤ መንግስትም ህብረተሰቡ የጸጥታ ስጋትን አስመልክቶ የሚሰጠውን መረጃ ተቀብሎ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥም ጠይቀዋል። የህብረተሰቡን ሠላም እያወከ በሚገኘው ሃሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ መንግስት አፋጣኝ የመፍትሔ እርምጃ መወሰድ እንዳለበትም ገልጸዋል።በተለይ ለህብረተሰቡ ቅርብ የሆኑ የጎጥ፣ ቀበሌ እና ወረዳ አደረጃጀቶች ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ አመልክተው ፤ የሚመደቡ አመራሮችም ንቁ፣ ታማኝ እና ሕዝቡን ያለአድሎ የሚያገለግሉ ሆነው መመረጥ አለባቸው ብለዋል። ከምንም በላይ የህብረተሰቡን አንድነት በማጠናከር ዘረኝነትን ማስወገድ እና አንድነቷ የተጠበቀች ኢትዮጵያን መፍጠር አጽንኦት እንዲሰጠው ነዋሪዎቹ ማመልከታቸውን አስተባባሪዎቹ አብራርተዋል።ነዋሪዎቹ በምክክር መድረኩ ለችግሩ ያነሷቸውን የመፍትሔ ሀሳቦች መንግሥት ተቀብሎ እንዲተገብርም ጠይቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38086
[ { "passage": "በቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ጳጉሜን 01/2012ዓ.ም የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ የኮማንድ ፖስቱን ሪፖርት በበለስ ከተማ ገምግመዋል።በንጹሃን ላይ በተከፈተ ጥቃት የሰዎች ሕይወት አልፏል። ሀብት ንብረት ወድሟል። አሁንም በሕይወትም ሆነ በሞት ያልተገኙ ሰዎች አሉ። ከ200 በላይ ሰዎች ቀያቸውን ለቅቀው ተሰድደዋል። በዞኑ ወቅት እየጠበቁ ጥቃት የሚፈጽሙ አሸባሪዎችን በተቀናጀ መንገድ ማስወገድ አለመቻል ነዋሪዎችን ለተጨማሪ ስጋት ዳርጓል።የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አትንኩት ሽቱ ባለፉት ዓመታት ከመንግሥት መዋቅር ውጭ በሆኑ ቀበሌዎች የተፈጠሩ ግጭቶች የአመራሩ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ደካማ መሆን ነው ብለዋል።በቡለን ወረዳ በንጹኃን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ፖሊስ ” ከአቅም በላይ ነው” ብለው በመውጣታቸው የተባባሰ ችግር መሆኑን ገልጸዋል። ተልዕኮን የመፈጸም ውስንነት ዋጋ ማስከፈሉን የተናገሩት አስተዳዳሪው የንጹሃን ሕይወት የቀጠፋ አሸባሪዎች ከዚህ አካባቢ የተፈጠሩ ነገር ግን ሕዝቡን የማይወክል ኃይሎች ድርጊት እንደሆነ ተናግረዋል። አሸባሪዎቹ ከመከላከያ፣ ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከጸረ ሽምቅ ተዋጊዎች አኩርፈው የወጡ፤ በኢንቨስትመንት ካሳ ያልረኩና ከመንግሥት የሥራ ኃላፊነት በሥራ ድክመት የተባረሩ ኃይሎች በህውሃት እየታገዙ፣ ከውጭ ሀገር እየተደገፉ የሚያሸብሩ ቡድኖች መሆናቸውን ተናግረዋል።የቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አሻድሊ ሐሰን “በቡለን ወረዳ ንጹሃን ላይ በተፈጠረው ግድያ ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል” ነው ያሉት። የሞቾች ቁጥር በማኅበራዊ ሚዴያው እንደሚቀርበው የተጋነነ አይደለም ያሉት አቶ አሻድሊ ዝርዝር መረጃው ምርመራ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።በቀጣይ የአካባቢውን የፀጥታ ኃይል ማደራጀት፣ ሽብሩን ከኋላ የሚደግፉ አካላትን መረብ መበጠስ፤ በየደረጃው ያሉ ኃላፊዎች በድርጊቱ እንዳላቸው ሚና ተጠያቂ ማድረግ እና አሸባሪዎችን በሕግ ቁጥጥር ስር ማዋል የትኩረት ነጥቦቻቸው መሆኑን ገልጸዋል።ሽፍቶቹ ለሽብር ዓላማቸው ሕዝቡን በማታለል ተባባሪ ማድረግ፣ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ መሆንና ከውጭ አካላት የሚያገኙትን ድጋፎችና ሴሎች፤ በመለየት ችግሩን ለመፍታት እንደሚሠሩም አስታውቀዋል።በምዕራብ ዕዝ 22ኛ ክፍለ ጦር 3ኛ ብርጌድ አዛዥና የጸጥታ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ኮሎኔል አያሌው በየነ ጥቃቱን ለመቆጣጠር የተቻለ ቢሆንም የማይመለስ የሰው ህይወትና ንብረት ወድሟል ብለዋል።", "passage_id": "eac1c3867207eac3154122d7dcb1e034" }, { "passage": "በመተከል በንፁሃን ላይ የደረሰውን ጥቃት ባለመከላከልም ሆነ በሌላ መልኩ ጥቃቱን የፈጸሙና ያባባሱ ሰዎችን ሕግ ፊት የማቅረብ ሂደት እንዲጀመር የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አሳሰበ።“የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ ነው ” በሚል በመተከል ዞን፣ ቡለን ወረዳ፣ በኩጂ ቀበሌ በንፁሃን ላይ የደረሰውን ጥቃት አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መግለጫ አውጥቷል።ኮሚሽኑ በመግለጫው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እተዳከመ መሄዱን በመግለጽ፤ የጥቃቱን ሂደት በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት እና ከተጎጂዎች ጋር በመነጋገር ሲከታተልና ሲያጣራ መቆየቱን አስታውቋል።ኮሚሽኑ ሁኔታውን እስካጣራበት ጊዜ ድረስ በቡለን ሆስፒታል 36 ተጎጂዎች እርዳታእየተደረገላቸው ሲሆን አብዛኞዎቹ በጥይት ሌሎቹ በቀስት የቆሰሉ መሆናቸውን አረጋግጧል በኩጂ ቀበሌ በሰው ሕይወት እና አካል ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ የደረሱ ሰብሎችና የተሰበሰቡ ማሳዎች በእሳት መጋየታቸውም ጭምር መረጃ እንደደረሰው ገልጿል።በድባጤ ወረዳ ዶንበን ቀበሌ ስጋት የገባቸው ነዋሪዎች ከታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ቀዬአቸውን ጥለው እየተሰደዱ እንደሆነም ኮሚሽኑ መረጃ አለኝ ብሏል በመግለጫው።በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚከሰቱ ጥቃቶችን ተደጋጋሚነትና የክልሉን ሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ሁኔታ አስመልክቶ፣ የፌዴራሉንና የክልሉን መንግሥታት የተጠናከረ ትብብርና ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሻ ኢሰመኮ ሲያሳስብ የቆየ ቢሆንም ጥቃቶቹ በመልክ እና በስፋት እየተባባሱ መምጣታቸው ነው የተገለጸው።በጥቃቱ ጉዳት ለደረሰባቸውን እና ለተፈናቀሉ ሰዎች የህክምና እና ሰብአዊ እርዳታ እንዲቀርብ እንዲሁም ተገቢው ማጣራትና ጥቃቱን ባለመከላከልም ሆነ በሌላ መልኩ ጥቃቱን የፈጸሙና ያባባሱ ሰዎችን ሕግ ፊት የማቅረብ ሂደት ከወዲሁ እንዲጀመርም ኮሚሽኑ አሳስቧል።በአካባቢው የሚገኘውን የፀጥታ ኃይልና መዋቅር የሰዎችን ደኅንነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በከፍተኛ ደረጃ በአፋጣኝ እንዲጠናከርም ኢሰመኮ ጥሪ አቅርቧል።", "passage_id": "af0886f2cc87b04dc065ec0a81efe4bb" }, { "passage": "አዲስ አበባ፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ጉባ ወረዳ በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት ያደረሰው ታጣቂ ኃይል በህውሓት ስልጠናና የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያገኙ የአማራ ክልል አስታወቀ። ዓላማው በብሄር ብህረሰቦች መካከል ግጭት በመፍጠር የአካባቢውን ሰላም ለማወክ መሆኑም ተመለከተ። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈትቤት ኃላፊ አቶ አገኘው ተሻገር በጥቃቱ ዙሪያ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ጥቃቱን የፈጸመው ኃይል በአካባቢው የብሔር ግጭት የመቀስቀስ ዓላማ በመያዝ ተደጋጋሚ የጥፋት ሙከራ ሲያደርግ የቆየ ነው። ታጣቂ ኃይሉ በህውሓት የስልጠናና የገንዘብ ድጋፍ እንደሚደረግለት አመልክተው፤ ህውሓት ሀገርን ለማተራመስ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ አካል መሆኑምን ጠቁመዋል። ድርጊቱ ከተፈጸመበት ጊዜ ጀምሮ አጥፊዎችን ፈልጎ ለመያዝና አስፈላጊውን ዕርምጃ ለመውሰድ የፀጥታ መዋቅሩ የተጠናከረ ጥረት እያደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል ።በአሁኑ ጊዜም አካባቢው ላይ ሰላም ሰፍኗል።አርሶአደሩም የእርሻ ሥራውን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡ ችግሩ የደረሰበት አካባቢ የአማራ ክልል አርሶአደሮች በስፋት የእርሻ ሥራ የሚያከናውኑበትና በቀን ሥራም ተቀጥረው የሚሠሩበት እንደሆነ የጠቆሙት አቶ አገኘሁ፤ በአማራ እና በጉሙዝ ብሄረሰብ መካከል ምንም ዓይነት ግጭት እንደሌለና ለዘመናት አብሮ የኖረ ህዝብ መሆኑም አስረድተዋል፡፡ ድርጊቱ በሰላም አብሮ\nየኖረውን ህዝብ ለማለያየት\nሆን ተብሎ የተፈጸመ\nመሆኑንም አመልክተዋል።ማን እንደፈጸመውም\nይታወቃልም።አጥፊውን ታጣቂ ኃይል\nህወሓት በገንዘብና በሥልጠና\nእንደሚያግዘውም አመልክተዋል፡፡ ጥቃቱ ህውሓት ለውጡን ወደቀውስ ለመለወጥ ምን ያህል አልሞ እየሠራ እንደሆነ የሚያሳይ ነው ያሉት ኃላፊው፤ ለህብረተሰቡ በችግሩ ዙሪያ ግንዛቤ በማስጨበጥ ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅ የማድረግ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ጠቁመዋል።በዚህም እስከአሁንም በአማራ ክልል የሽብር ተግባር ለማከናወን ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከ95 በላይ ፀጉረ ልውጥ ሰዎችን መያዛቸውን አመልክተዋል፡፡ በአጥፊ ታጣቂ ኃይል ሕይወታቸው ያለፈ የአማራ ክልል አርሶአደሮች 12ቱ ከምዕራብ ጎጃም፣ ሁለቱ ደግሞ ከጎንደር መሆናቸውንና የሁሉም አስክሬን ለቤተሰብ ተሰጥቶ በክብር የቀብራቸው ሥነሥርዓት መፈጸሙን ገልጸዋል።አርሶአደሩ በተፈጸመው ነገር ሳይደናገጥ የወቅቱን የእርሻ ሥራ እንዲያከናውንም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል\nየሠላም ግንባታ እና\nጸጥታ ቢሮ ምክትል\nኃላፊ አቶ አብዱላዚዝ\nመሀመድ በመተከልዞን ጉባ ወረዳ ከሀገር ውጭና ከውስጥ ተልዕኮ የተሰጣቸው የጥፋት ኃይሎች ሐምሌ 20 ቀን 2012 ምሽት አካባቢ አቡጃር ቀበሌ ባደረሱት ጥቃት የ14 ንጹሐን ዜጎች ሕይወት ማለፉን ከትናንት በስቲያ ማሳወቃቸው ይታወሳል፡፡ በወቅቱም የጥፋት ቡድኑ ተገቢ ስልጠናና ተልዕኮ በመያዝና በከባድ መሳሪያ በመታገዝ በተለይም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት የማስተጓጎል እና የብሔር ግጭት የመቀሳቀስ ዓላማ በመያዝ ተደጋጋሚ የጥፋት ሙከራ ሲያደርግ መቆየቱንም ገልጸዋል፡፡ የክልሉ የጸጥታ ኃይል\nከመከላከያ ሠራዊትና ከፌዴራል\nፖሊስ ጋር በጋራ\nበመሆን ቀደም ብሎ\nበአካባቢው ሠላምን ለማረጋገጥ\nዕርምጃ ሲወስድ መቆየቱን\nአመልክተዋል። በጥፋት ቡድኑ\nላይ እየተወሰደ ካለው\nዕርምጃ በተጨማሪ አራት\nተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር\nስር መዋላቸውን ጠቁመዋል።\nሕግን የማስከበር ዕርምጃዎች\nበአካባቢው ተጠናክሮ መቀጠሉንም\nአስታውቀዋል፡፡አዲስ ዘመን ሐምሌ 23/2012 በጋዜጣው ሪፖርተር", "passage_id": "02b9f47004abfb732a05ece9249af780" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 22 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚሠራ ክልል አቀፍ የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተቋቁሟል፡፡", "passage_id": "39efbb08c3ede012fd00c642e461a013" }, { "passage": "በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚደርሰውን የንፁኃን ዜጎች ግድያ ከዚህ በላይ በትዕግስት እንደማይመለከተው የአማራ ክልል መንግሥት አስታውቋል፡፡ ዜጎች በግፍ የሚገደሉበት ጊዜ ማብቃት እንዳለበትም ክልሉ አሳስቧል፡፡\nበመተከል ዞን የተፈጸመውን ግድያ በተመለከተ የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ግዛቸው ሙሉነህ \"በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘርን መሠረት ያደረገ ጥቃት ተፈፅሟል\" ማለታቸውን ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል፡፡\nበክልሉ የሚስተዋለውን ጥቃት ለማስቆም ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልና ከፌዴራል መንግሥት ጋር በጋራ እንደተሠራ የተናገሩት አቶ ግዛቸው የክልሉ መንግሥት ለተጎዱ ዜጎች ቦታው ድረስ በመሄድ ድጋፍ ማድረጉንም አስታውሰዋል፡፡ ይሁን እንጂ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለው ችግር መቀጠሉን ነው የገለጹት፡፡\nበመተከል ዞን በዳንጉር፣ ጉባ፣ ማንዱራ፣ ወንበራና ቡለን ወረዳዎች በታቀደና በተደራጀ የታጠቀ ኃይል \"ወገኖቻችን ላይ ጥቃት ተፈጽሟል\" ብለዋል፡፡\nጥቃት አድራሾቹ ዓላማቸው አድርገው የሚንቀሳቀሱት ብሔርን ከብሔር ጋር ማጋጨት እንደሆነና ቀጣናውን በተለይም አማራ ክልልን ማተራመስ መሆኑንም አቶ ግዛቸው ተናግረዋል፡፡\nከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ውይይቶች ተደርገው \"አቅጣጫ ቢቀመጥም እስካሁን ድረስ መሬት ላይ አልወረዱም\" ያሉት አቶ ግዛቸው \"የቤንሻንጉል ክልል መንግሥት መዋቅር ንጹሕ አለመሆን እና ዜጎችን ያገለለ ሥራ መሥራቱ ለችግሩ ምክንያት ነው\" ብለዋል፡፡ \"የማዕከላዊ መንግሥቱም ቢሆን ያደረገው ጥረት ጥሩ ቢሆንም ዜጎችን ግን ከሞት እያዳነ አይደለም\" ብለዋል፡፡\nበአማራ ክልል መንግሥትም ቢሆን ችግሮችን በውይይትና በዴሞክራሲ ለመፍታት ብዙ የተደከመ ቢሆንም ነዋሪዎችን \"ከጥቃት መታደግ አልተቻለም\" ነው ያሉት፡፡\nበመሆኑም በቀጣይነት ሁለት ምርጫዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ አንደኛው የቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ጉዳዩን \"በዋዛ ፈዛዛ ሳይመለከተው\" የአማራ ክልል ተወላጆችን እንደሌላው የክልሉ ነዋሪ በሰላም እንዲኖሩ የማደራጀት፣ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ገብተው ራሳቸውን እንዲከላከሉ የሚያስችል ሥራ መስራት እንደሆነ ነው የተናገሩት፡፡\nሁለተኛው አማራጭ ግን \"የቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል እርምጃ እስኪወስድ ብቻ አንጠብቅም ብዙ ታግሰናል፤ እንደ አማራ ክልል ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመሆን አሠራሩ የሚፈቅደውን ሁሉ በማድረግና ከቤኔሻንጉል ክልል መንግሥት ጋር በጥምረት በመሥራት የክልሉ ተወላጆች ከዚህ በኋላ ከጥፋት የመታደግ ሁኔታ የግድ ነው\" ብለዋል፡፡\nየክልሉ ሕዝብም ከስሜታዊነት በመውጣት መንግሥትን መደገፍ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ የአማራ ክልል መንግሥት የራሱን ሥራ ለመሥራት አቋም የወሰደ ስለሆነ ጉዳዩን በሰከነ መንገድ እንዲደግፈውም ጥሪ አቅርበዋል፡፡\n", "passage_id": "42e80eb16f5e5be2c8f08e7c34d55f03" } ]
cd495016ee848e3af4b26c3eaafedcb4
b79dd0302fad1d7113c4fc94ff167862
ሜጀር ጄኔራል ከድር አራርሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- የሰሜን እዝ ምክትል አዛዥና የሎጂስቲክስ ኃላፊ የነበሩት ሜጀር ጀኔራል ከድር አራርሳ ትናንት ፍርድ ቤት ቀረቡ።እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ሜጀር ጀኔራል ከድር አራርሶ የሰሜን እዝ የጦር መሳሪያ በሕወሓት ልዩ ኃይል እንዲዘረፍ መረጃ ሰጥተዋል በሚል ወንጀል ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፤ ትናንት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል። እንደ ዘገባው፣ ተጠርጣሪው የሰሜን እዝ ምክትል አዛዥና የሎጂስቲክስ ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ በነበረበት ጊዜ ከሕወሐት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ግንኙነት በመፍጠር መረጃ ሲሰጡ ነበር ተብሏል። ከዚህ በፊት በእዙ ስር ያሉ መሳሪያዎችን ከአካባቢው ለማንሳት ሙከራ በተደረገበት ወቅት እንቅስቃሴው እንዲሰናከል ስለማድረጋቸው መረጃ ማሰባሰቡን መርማሪ ፖሊስ ለችሎቱ አብራርቷል። ተጠርጣሪው ከህወሓት ቡድን ጋር ባላቸው ግንኙነት በአድሏዊ አሰራር በተደጋጋሚ የውጭ አገር እድል ይሰጣቸው እንደነበርም ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ገልጿል። በመሆኑም ፖሊስ ለቀሪ የምርመራ ስራዎች 14 ቀን እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል። ተጠርጣሪው በበኩላቸው “በተባለው ጉዳይ ጥፋት የለብኝም ፍርድ ቤቱ በነፃ ያሰናብተኝ” ሲሉ ጠይቀዋል።የግራ ቀኝ ክርክሩን ያደመጠው ችሎቱ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀን 11 ቀን በመፍቀድ ለታሕሳስ 26 ቀን 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38071
[ { "passage": "በተከሰሱበት የሙስና ወንጀል በመዝገብ ቁጥር 141352 ላይ መከላከያ ምስክሮቻቸውን በማሰማት ላይ የሚገኙት፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተርና ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣ የቀድሞ ፍትሕ ሚኒስትርና ሚኒስትር ዴኤታን በመከላከያ ምስክርነት አሰሙ፡፡ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 15ኛ ወንጀል ችሎት ለአቶ መላኩ ፈንታና አቶ ገብረ ዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ መከላከያ ምስከር ሆነው ዓርብ ታኅሳስ 13 ቀን 2010 ዓ.ም. ቀርበው የመሰከሩት፣ የቀድሞ የፍትሕ ሚኒስትር አቶ ብርሃን ኃይሉና ሚኒስትር ዴኤታ የነበሩት አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ናቸው፡፡ ምስክሮቹ በመከላከያ ምስክርነት የቀረቡት፣ እነሱ በሥልጣን ላይ በነበሩበት ከ2001 ዓ.ም. እስከ 2005 ዓ.ም. መንግሥት የታክስ ሥወራን ለመቆጣጠር በ1,000 ነጋዴዎች ላይ ጥናት ሲያደርግ፣ ከዘጠኝ እስከ አሥር የሚሆኑ ነጋዴዎች አራጣ ማበደራቸው በመታወቁ ባለሥልጣኑ ክስ እንዲመሠርትባቸው ውክልና ሲሰጠው፣ የኬኬ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ባለቤትና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከተማ ከበደ ተካተው የተላኩ ቢሆንም፣ ከአቶ መላኩና አቶ ገብረ ዋህድ ጋር ባላቸው የጥቅም ግንኙነት እንዳይከሰሱ አድርገዋቸዋል በማለት ዓቃቤ ሕግ በመሠረተው ክስ ላይ መከላከያ ምስክርነታቸውን እንዲያሰሙ መሆኑን፣ አቶ መላኩ በጠበቃቸው አማካይነት ጭብጥ አስይዘዋል፡፡ አቶ ብርሃን በእውነት ለመመስከር ቃለ መሐላ ከፈጸሙ በኋላ በሰጡት ምስክርነት እንደገለጹት፣ የፍትሕ ሚኒስትር ሆነው የሠሩት ከ2001 ዓ.ም. እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ ነው፡፡ እሳቸው በሠሩባቸው ዓመታት መንግሥት በ1,000 ነጋዴዎች ላይ ጥናት አላደረገም፡፡ ሐሳቡም ሆነ ዕቅድም አልነበረውም፡፡ ነገር ግን የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የታክስ ሥራውን ለመከላከል በ1,000 ድርጅቶች (ባለሀብቶች) ላይ ጥናት ማድረጉን እንደሚያውቁ ተናግረዋል፡፡ ባለሥልጣኑ ጥናቱን ሲያደርግ ሰባት ባለሀብቶች ከፍተኛ ገንዘብ (ሀብት) እንዳላቸው በማወቁ፣ የገንዘቡ ምንጭ ከየትና ምን እንደሆነ ለማወቅ ተጨማሪ ጥናት ሲያደርግ፣ አራጣ ሆኖ እንዳገኘው መስማታቸውንም አቶ ብርሃን መስክረዋል፡፡ በመሆኑም አራጣ ወንጀል ቢሆንም፣ ባለሥልጣኑ ክስ ለመመሥረት ሥልጣን ስለሌለውና ሥልጣኑ የፍትሕ ሚኒስቴር በመሆኑ ውክልና መጠየቁን አብራርተዋል፡፡ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን አራጣ በማበደር ከባንክ ወለድ በላይ ከፍተኛ ወለድ እንደሚያስከፍሉ የደረሰባቸውን ሰባት ተጠርጣሪዎች በመግለጽ፣ ውክልና እንዲሰጠው በባለሥልጣኑ የዓቃቤ ሕግ ዋና ዳይሬክተር በነበሩት አቶ እሸቱ ወልደ ሰማያት አማካይነት ማቅረቡን አቶ ብርሃን መስክረዋል፡፡ አቶ እሸቱ ጥያቄውን ያቀረቡት ለሚኒስትር ዴኤታው አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ መሆኑን ያስታወሱት አቶ ብርሃን፣ በአቶ ብርሃኑ ፊርማ ውክልናው ለአቶ እሸቱ መሰጠቱንና ለእሳቸው በግልባጭ እንዲያውቁት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በተሰጠው አራጣ አበዳሪዎችን የመክሰስ ውክልና ውስጥ የአቶ ከተማ ከበደ ስም ተካቶ ስለመላኩ ተጠይቀው፣ አቶ ከተማን በሚመለከት ስለመሰጠቱ እንደማያስታውሱ፣ ነገር ግን በተገለጸው ዝርዝር ውስጥ እንዳልተካተቱና ተካተው ቢሆን ኖሮ በዝርዝሩ ውስጥ ይታዩ እንደነበር በመግለጽ አለመካተታቸውን መስክረዋል፡፡ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬም ቀርበው በሰጡት ምስክርነት፣ መንግሥት በ1,000 ነጋዴዎች ላይ ምንም ዓይነት ጥናት እንዳላካሄደ፣ ጥናቱ የተካሄደው በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መሆኑን ገልጸው፣ በጥናቱ አራጣ አበዳሪዎችን በማግኘቱ፣ ክስ ለመመሥረት ከፍትሕ ሚኒስቴር ውክልና መውሰዱን አስረድተዋል፡፡ ውክልናውን በስማቸው ጠይቀው (ባለሥልጣኑን ወክለው)፣ ፈርመው የወሰዱት አቶ እሸቱ መሆናቸውን አረጋግጠው፣ ውክልናውን ፈርመው የሰጡት እሳቸው መሆኑንም መስክረዋል፡፡ ለሚኒስትሩም በግልባጭ ማሳወቃቸውንም አክለዋል፡፡ የመክሰስ ውክልና ሲሰጥ በቀረበላቸው ዝርዝር ውስጥ የአቶ ከተማ ከበደ ስም መካተት አለመካተቱን ተጠይቀው፣ የቀረበላቸው የሰባት ሰዎች ዝርዝር መሆኑንና በዚያ ውስጥ የአቶ ከተማ ስም እንደሌለ አስረድተዋል፡፡ ምስክሮቹ ምስክርነታቸውን እንዳጠናቀቁ ዓቃቤ ሕግ በተለይ ለአቶ ብርሃን ኃይሉ መስቀለኛ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ፍትሕ ሚኒስቴር ለባለሥልጣኑ በሰጠው ውክልና ላይ ከሰባቱ ተጠርጣሪዎች ጋር አቶ ከተማን ስምንተኛ አድርጎ ቢልክ ኖሮ፣ ክስ ሊመሠረትባቸው ስለመቻሉና አለመቻሉ ሲጠይቅ ተከሳሾች ተቃውሞ አቅርበዋል፡፡ ከላይ በጭብጥ ያስመዘገቡትን ክስ ዓቃቤ ሕግ አቅርቦና አስመስክሮባቸው፣ እንዲሁም ተከላከሉ እንዲባሉ አድርጎ በመስቀለኛ ጥያቄ እንዴት ‹‹ቢሆን ኖሮ›› የሚል ጥያቄ ሊያቀርብ ይችላል የሚል ተቃውሞ አቶ መላኩ ለፍርድ ቤቱ አቅርበዋል፡፡ በብይን ይመዘናል እየተባለ ቀደም ብሎ የተሰጠ ምስክርነት ሳይመዘን መታለፉን በማስታወስ፣ ‹‹ቢሆን ኖሮ›› የሚለው ጥያቄ በችሎቱ ተቀባይነት የሚያገኝ ከሆነ፣ የመከላከያ ምስክርነት ማሰማታቸው ጥቅም እንደሌለው ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የዓቃቤ ሕግን ጥያቄ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ ሌላው በመከላከያ ምስክርነት የቀረቡት የቀድሞ የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዓቃቤ ሕግ የነበሩትና በእስር ላይ የሚገኙት አቶ መርክነህ ዓለማየሁ ናቸው፡፡ አቶ መርክነህ እንደመሰከሩት፣ የተቋሙ ሥልጣን የሚመነጨው ከተቋቋመበት አዋጅ ቁጥር 587/2000 ነው፡፡ ሥልጣኑም የታክስና ጉምሩክ ወንጀሎች ሲከሰቱ ይከሳል፡፡ በሥራ ሒደት በሌላ ተቋም ሥልጣን ሥር የሚወድቁ የወንጀል ግኝቶች ሲያጋጥሙት ውክልና ወስዶ ይከሳል፣ ይከራከራል፣ ያስወስናል፡፡ ነገር ግን ለመመርመር አይነሳሳም፣ አይመረምርም፡፡ በ2001 ዓ.ም. በተደረገ ጥናት አራጣ አበዳሪዎች በመገኘታቸው ከፍትሕ ሚኒስቴር ውክልና ወስዶ መክሰሱንና ማስቀጣቱን ገልጸዋል፡፡ አራጣ በማበደር ከባንክ ወለድ በላይ ወለድ ሲያስከፍሉ የነበሩት አቶ አየለ ደበላ፣ አቶ ከበደ ተሠራ፣ አቶ ሌንጫ ዘገየን ጨምሮ ሰባት ግለሰቦች መከሰሳቸውን ጠቁመው፣ አቶ ከተማ ከበደ ግን በዝርዝሩ ውስጥ እንደሌሉና በሳቸውም ላይ ከፍትሕ ሚኒስቴር የተሰጠ ውክልና እንዳልነበረ መስክረዋል፡፡ በባለሥልጣኑ ዓቃቤ ሕግ ሥራ ውስጥ የአቶ መላኩም ሆኑ የአቶ ገብረ ዋህድ ምንም ዓይነት ጣልቃ ገብነት እንደሌለበት፣ ከማንኛውም ነገር ነፃ ሆኖ ይሠራ እንደነበርና ከተፅዕኖ ነፃ መሆኑን አክለዋል፡፡ለአቶ ከተማ ከበደ መከላከያ ምስክር ሆነው የተቆጠሩት አቶ ባህሩ አብርሃ ለመመስከር የቀረቡ ቢሆንም፣ የቀረበላቸውን ጥያቄ ‹‹አላውቅም፣ አልሰማሁምና አብሬ አልነበርኩም፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ነገር ግን የአቶ ከተማ ጠበቆች ለፍርድ ቤቱ እንዳመለከቱት፣ ምስክሩ ከአቶ ከተማ ጋር በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል  ታስረው ብዙ ሚስጥሮችን ለአቶ ከተማ መናገራቸውንና በምርመራ ወቅትም ለፖሊስ የሰጡት ቃል የተመዘገበ መሆኑን ገልጸው፣ ሰነዱ እንዲታይላቸው አመልክተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ሰነዱን እንደሚያየው አስታውቋል፡፡ ሌሎች አራት የመከላከያ ምስክሮች ለአቶ መላኩ፣ ለአቶ ገብረ ዋህድና ለአቶ ከተማ ቀርበው ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡  ምስክሮቹ አቶ ጥሩነህ በርታ በወቅቱ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የኢንተለጀንስ ቡድን መሪ፣ አቶ ቁምላቸው ሻምበል የኢንተለጀንስ ሠራተኛ መሆናቸውን ገልጸው፣ ከታክስ ሥወራ ጋር በተያያዘ ስለተደረገ ክትትልና ከፍተኛ ገቢ እያንቀሳቀሱ አነስተኛ ግብር ስለሚከፍሉ ሰዎች ጥናት ተደርጎ እንደተደረሰባቸው መስክረዋል፡፡ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩም ለባንኮችና ለውል ክፍል በጻፏቸው ደብዳቤዎች የተገኙ የብድር ሰነዶችና የባንክ ስቴትመንት ማስረጃዎች የገንዘቡ ምንጭ አራጣ መሆኑ ታውቋል፡፡ ከንግድ ድርጅቶቻቸውና ከመኖሪያ ቤታቸው በብርበራና በፍተሻ የተገኙ ማስረጃዎች ተተንትነው ክስ እንዲቀርብባቸው ለምርመራ ቡድን እንዲተላለፍ መደረጉንም አስረድተዋል፡፡ የክትትል ሥራው በዋናው ዳይሬክተርና በበላይ አካል ቁጥጥር የሚደረግበት ስለሆነ፣ ከፌዴራል ፖሊስና ከመርማሪዎች ጋር ፍተሻና ብርበራ እንደተከናወነ ገልጸዋል፡፡ የክትትሉን ሥራ ሚስጥራዊነት ለመጠበቅ፣ ዓቃቤ ሕግም ሆነ ሌላ ወገን ጣልቃ የማይገባበት መሆኑንና ምርመራው ከተጠናቀቀ በኋላ ጉዳዩ ለዓቃቤ ሕግ እንደቀረበ መስክረዋል፡፡ አቶ ጥሩነህ እንደገለጹት፣ ለክትትልና ለምርመራው መነሻ የነበረው ከታክስ ሥወራ ጋር የተያያዘ ጉዳይ ብቻ ነበር፡፡ በሒደት ግብር የማይከፍሉና አነስተኛ ግብር የሚከፍሉ ተጠርጣሪዎች የሚያንቀሳቅሱት ገንዘብ ምንጩ አራጣ መሆኑን የሚያመለክት ማስረጃ ከቀረበ በኋላ፣ አቶ መላኩ ለባንክና ለውል ክፍል ማስረጃ እንዲላክ በተጻፈው ደብዳቤ፣ የምርመራና የክትትል ሥራ በሚከናወንበት ጊዜ አቶ ከተማ ከበደ ወይም ልጃቸው ትዕግሥት ከተማ እንዳልነበሩ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡አቶ ደግአደረገ ሥዩም የተባሉ አማራ ልማት ማኅበር የጽሕፈት ቤት ኃላፊም እንደመሰከሩት፣ ማኅበሩ የመክፈቻ በዓል ያከበረው ጥቅም 15 ቀን 2002 ዓ.ም. በሒልተን ሆቴል ነው፡፡ በዚሁ ዕለት አቶ መላኩ ፈንታና አቶ ከተማ ከበደ እንዳልነበሩ ተናግረዋል፡፡ ጥር 28 ቀን 2002 ዓ.ም. ባህር ዳር በነበረው የዕርዳታ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ግን መገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ የምሳ ግብዣ የተደረገው በማኅበሩ ጽሕፈት ቤት እንጂ ዓባይ ምንጭ ሆቴል እንዳልነበረም መስክረዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ታኅሳስ 8 ቀን 2010 ዓ.ም. በወጣው ዕትም አቶ መላኩ ፈንታ በቁጥጥር ሥር በነበሩበት ጊዜ መርማሪ፣ ‹‹አቶ ከተማ ከበደን ያልከሰስከው ለአማራ ልማት ድርጅት አሥር ሚሊዮን ብር ስለሰጠህ ነው፤›› የሚል ጥያቄ አቅርቦላቸው እንደነበርና አቶ ከተማ የምስክርነት ቃላቸውን ሲሰጡ ግን፣ አሥር ሚሊዮን ብር በጥሬ ገንዘብ ለመስጠት ቃል እንዳልገቡ ገልጸው ነበር፡፡ አቶ ከተማ በምስክርነት እንዳረጋገጡት፣ በአማራ ክልል በሚሰጣቸው ባዶ ቦታ ላይ በአሥር ሚሊዮን ብር ወጪ ትምህርት ቤት ለመሥራት ቃል መግባታቸውን ነው፡፡ ለትምህር ቤት ግንባታ የሚውል መሬትም እንዲሰጣቸው በተደጋጋሚ ጠይቀው ማግኘት ስላልቻሉ፣ የተባለውን ትምህርት ቤት መሥራት አለመቻላቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልጸው ነበር፡፡ በተጨማሪም አቶ መላኩ ፈንታ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር በነበራቸው ውይይት፣ ፕሮቶኮል ጠብቆ በየግብዣው ላይ መታየትና የድርሻን ወስዶ መሄድን እንደማይቀበሉ አስረድተው፣ የእሳቸው ድጋፍ የማይለያቸው ከሆነ፣ ተቋሙን በኃላፊነት መምራትና የታክስ ሪፎርም ጥናት ለማካሄድ ፈቃደኛ መሆናቸውን፣ ያቀረቡት ሐሳብ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቀባይነት አግኝቶ ወደ ሥራ መግባታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡           ", "passage_id": "975a509689b181ce40f97f84a453d40e" }, { "passage": "የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 10ኛ ወንጀል ችሎት በከባድ የሙስና ወንጀል በተጠረጠሩት በሜጄር ጄነራል ክንፈ ዳኘው ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ለፖሊስ ፈቀደ፡፡ፍርድ ቤቱ በከፍተኛ የስብዓዊ መብት ጥሰት፣ በተጠረጠሩት በአቶ ተስፋዬ ውርጌ ጉዳይ ላይም ተመሳሳይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ", "passage_id": "1cb7ef6d9b5264ff95f2801ef3caab64" }, { "passage": "የብሔራዊ መረጃ ደኅንነት አገልግሎት የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ነበሩ የተባሉና በቱርክ ኢስታምቡል ለሥራ ተመድበው በመጠባበቅ ላይ የነበሩት አቶ መአሾ ኪዳኔ፣ በከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረው ከታሰሩ በኋላ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ሌላው ተጠርጣሪ አቶ ሀዱሽ ካሳም አብረዋቸው ቀርበዋል፡፡አቶ መአሾ በተጠረጠሩበት ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በቁጥጥር ሥር የዋሉት ቅዳሜ ኅዳር 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ከመኖሪያ ቤታቸው መሆኑን ጠቅሶ፣ የፌዴራል  ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ሰኞ ታኅሳስ 1 ቀን 2011 ዓ.ም. የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አሥረኛ ወንጀል ችሎት አቅርቧቸዋል፡፡ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ነበሩ የተባሉት አቶ መአሾ፣ በወቅቱ በፓርላማ በሽብርተኝነት ተፈርጀው የነበሩት የኦነግና የአርበኞች ግንቦት ሰባት አባል ናቸው ተብለው በሐሰት የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ፣ ለበታች ሠራተኞች ትዕዛዝ መስጠታቸውን መርማሪ ቡድኑ አስረድቷል፡፡ በሐሰተኛ ማስረጃ በቁጥጥር ሥር የሚውሉትን ዜጎች ዓይናቸውን ሸፍኖ በማሰር በሥውርና በሕግ ባልፈቀደ ቦታ በማሰር ከቤተሰብ እንዲደበቁ ማድረጋቸውን፣ በመደብደብና በተለያዩ ማሰቃያ ነገሮች ከፍተኛ የሆነ ሥቃይ እንዳደረሱባቸውም መርማሪ ቡድኑ ተናግሯል፡፡ ተጠርጣሪው ከገቢያቸው በላይ ሦስት ቤቶች መገንባታቸውንና ምንጩ ያልታወቀ ሀብት አከማችተውና ለባለቤታቸው ውክልና ሰጥተው በመገኘታቸው በሙስና ወንጀልም እንደጠረጠራቸው አስረድቷል፡፡ መርማሪ ቡድኑ በተመሳሳይ ቀን በቁጥጥር ሥር እንዳዋላቸው ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት ያቀረባቸው፣ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የኦፕሬሽን ክፍል ዳይሬክተር መሆናቸው የተገለጸው አቶ ሀዱሽ ካሳ ናቸው፡፡ መርማሪ ቡድኑ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አሥረኛ ወንጀል ችሎት እንዳስረዳው፣ እሳቸውም በተመሳሳይ ሁኔታ የኦነግና የአርበኞች ግንቦት ሰባት አባል ሳይሆኑ በሐሰት አባል መሆናቸው እየተገለጸ በቁጥጥር ሥር የዋሉ በርካታ ዜጎች በሥውር እስር ቤት እንዲታሰሩ፣ ከቤተሰብ በመደበቅ እንዳይገናኙ በማድረግ፣ ድብደባ በመፈጸም፣ የተለያዩ ማሰቃያ ዘዴዎችን በመጠቀም ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዲፈጸምባቸው ማድረጋቸውን ገልጿል፡፡ ተጠርጣሪው ከገቢያቸው በላይ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ማከማቸታቸውንም በመግለጽ፣ በሙስና ወንጀል መጠርጠራቸውንም አክሎ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡  ተጠርጣሪዎቹ፣ ምንም እንኳን የሕግ ዕውቀት ባይኖራቸውም ለጊዜው በራሳቸው መልስ ሰጥተው፣ በቀጣይ ቀጠሮ የመንግሥት ሠራተኛና ደመወዝተኛ በመሆናችን መንግሥት ተከላካይ ጠበቃ ያቆምልናል በማለት ለፍርድ ቤቱ ከገለጹ በኋላ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ አቶ መአሾ እንደገለጹት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አገሪቱን መምራት ከጀመሩ ወዲህ፣ በቱርክ ኢስታምቡል ለሥራ ተመድበዋል፡፡ የዲፕሎማሲ ሥልጠናም ወስደው የሚሄዱበትን ቀን በቤታቸው ሆነው እየተጠባበቁ እያለ፣ ‹‹በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረሃል›› ተብለው መታሰራቸውን አስረድተዋል፡፡ በተቋሙ ውስጥ ረዥም ዓመታት የሠሩ ቢሆንም፣ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች እንጂ የልዩ ጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ሳይሆኑ የሌላ ክፍል ዳይሬክተር መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ‹‹የተከሰስኩበትና በቁጥጥር ሥር እንድውል የተደረገበት ምክንያት ሁለት ነው፡፡ አንደኛው የትግራይ ተወላጅ መሆኔ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በፖለቲካ ውሳኔ ነው፤›› ብለዋል፡፡ ከዚህ ውጪ እሳቸው ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ሥነ ምግባራቸውን ጠብቀው የሚሠሩ መሆናቸውንና በዚህም የምሥጋና ቅፅል ስም የተሰጣቸው ንፁህ ሠራተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ አሳሪም፣ መርማሪም ሆነ ከዚህ ጋር የተገናኘ ሥራ ሠርተው እንደማያውቁና ዶሴ ተቀናብሮ የቀረበባቸው ክስ እንደማይመለከታቸው ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል፡፡ ‹‹እየተደረገብኝ ያለው ነገር ሞራሌንና ሰብዕናዬን ለመንካት እንጂ፣ እውነተኛ መጠርጠሪያ ድርጊት ሆኖና መቀጣጫ በማድረግ በመሆን ሌሎችን ዜጎች የሚቀርፅ አይደለም፤›› ብለዋል፡፡ የሥራ ባልደረቦቻቸው ቀደም ብሎ ሲያዙ እውነተኛ ተጠርጣሪ ቢሆኑ ኖሮ እሳቸውም ሊያዙ ይችሉ እንደነበር ጠቁመው፣ እንኳን ሰው ሊያስደበድቡና ሰብዓዊ የመብት ጥሰት እንዲፈጸም ሊያደርጉ ቀርቶ፣ ‹‹ሰደበኝ የሚል ካለ ይቅረብ፤›› በማለት ዕንባና ሳግ እየተናነቃቸው ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያንና ሕዝቧን እንዳያገለግሉ የማግለል ሥራ እየተሠራባቸው መሆኑንም አክለዋል፡፡ ንፁህና ታታሪ ሠራተኛ መሆናቸውን ገልጸው፣ ከቀድሞ የፌዴራል ፖሊስ ዳይሬክተር ጄኔራል ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) መሸለማቸውንና አሁን በቅርቡም የዲፕሎማሲ ሥልጠና ወስደው ቱርክ ኢስታምቡል መመደባቸውም፣ ጥሩና ብቁ ሠራተኛ መሆናቸውን የሚመሰክር እንጂ በዶሴ ተዘጋጅቶ እንደቀረበባቸው ያለ ሰብዕና እንደሌላቸው ምስክር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ‹‹እኔ ችሎት ቀርቤ ይኼ ዶሴ ሲነበብልኝ አዝኛለሁ፡፡ እኔ ታጋይ ነኝ፡፡ ሁለት ሦስት ጊዜ ቆስያለሁ፡፡ ይኼንን የማደርግ አይለሁም፤›› በማለት ይህንን ያደረጉ አካላት በቂምና በቀል በእሳቸው ላይ ለመሥራት አስበው ያደረጉት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከገቢ በላይ ሀብት ስለማከማቸታቸው በሰጡት ምላሽ፣ በመሥሪያ ቤታቸው ተደራጅተው እየሠሩት ያለ 72 ካሬ ሜትር ጅምር መኖሪያ ቤት ብቻ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ ይኼንንም ውክልና ለቤተሰቦቻቸው የሰጡት ለሥራ ወደ ውጭ (ቱርክ) በመመደባቸው እንጂ፣ በሐሰት እንደተቀነባበረባቸው ክስ አለመሆኑን አክለዋል፡፡ ‹‹እናውቀዋለን በፌስቡክ ገጽ ሳይቀር ዘመቻ ተከፍቶብናል፡፡ የተጻፈው ዶሴ ለምንም አይጠቅምም፡፡ የትም የምሸሽ አይደለሁም፡፡ ብጠራ የምቀርብ ነኝ፡፡ በመሆኑም ዋስትናዬ ይጠበቅልኝ፤›› በማለት ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ አቶ ሀዱሽ በበኩላቸው በሰጡት ምላሽ፣ በኢሚግሬሽን ሥራዎች በሞያሌና በተለያዩ ጠረፎች ተመድበው ሲሠሩ የኖሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ምንም ዓይነት ኃላፊነት የሌላቸውና ተራ ሠራተኛ እንደነበሩም አክለዋል፡፡ ወደ ኃላፊነት የመጡት ከሁለት ዓመት ወዲህ መሆኑን ጠቁመው፣ ይኼም የዋናው መሥሪያ ቤት የኦፕሬሽን ኃላፊነት ማለትም የፅዳት፣ የአትክልተኛና የትራንስፖርት ሥምሪት ኃላፊ ሆነው እየሠሩ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ በሕይወታቸው ምንም ዓይነት ወንጀል ሠርተው እንደማያውቁ ተናግረው፣ የዚህ ዓይነት ወንጀል ከየት እንደመጣባቸው እንደማያውቁም ገልጸዋል፡፡ ማንም እንደሚያውቃቸውና የተባለው ሁሉ እንደማይመለከታቸው አክለዋል፡፡ ‹‹እየወረደብኝ ያለው ጥቃት ነው፤›› ብለዋል፡፡ ከባለቤታቸው ጋር የተፋቱ ቢሆንም ሁለት ልጆቻቸውን በጋራ እያሳደጉ መሆናቸውን፣ የልጆቻቸው እናት ዳቦና እንጀራ ጋግራ እየሸጠች ሕይወቷን እየመራች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን መርማሪ ቡድን የእሷንና የእሳቸውን የባንክ ቡክና ለልጆች ትምህርት ቤት የሚከፈል አሥር ሺሕ ብር መውሰዱን በመገለጽ፣ እንዲመለስላቸው ጠይቀዋል፡፡ ገንዘቡን የወሰዱት ቤታቸው በተበረበረበት ወቅት መሆኑን አሳውቀዋል፡፡ ከገቢ በላይ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት እንዳፈሩ የተገለጸው፣ አንድ ኮንዶሚኒየም ቤት ደርሷቸው መክፈል ስላቃታቸው ከማከራየታቸው ውጪ ሌላ ነገር እንደሌላቸው አስረድተዋል፡፡ የዋስትና መብታቸው እንዲጠበቅላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡  መርማሪ ቡድኑ ተጠርጣሪዎቹ የጠየቁትን ዋስትና ተቃውሞ ምክንያቱን አስረድቷል፡፡ አቶ መአሾ የታሰሩት ‹ትግሬ ስለሆኑ ወይም በፖለቲካ ውሳኔ› አለመሆኑ፣ ፖሊስ ሕግ ማስከበር እንጂ ከፖለቲካ ጋር የሚያገናኘው ነገር እንደሌለ አስረድቷል፡፡ ሕገ መንግሥቱንና የአገሪቱ ሕጎችን የጣሰ ድርጊት በመፈጸም ስለተጠረጠሩ እንጂ፣ እሳቸው ስላሉት ነገር የሚያውቀው ነገር እንደሌለም አክሏል፡፡ አቶ ሀዱሽ ከባለቤታቸው ጋር ለመፋታታቸው የተናገሩትን በሚመለከት፣ እንደተፋቱ በማስመሰል የማዘጋጃ ቤት ወረቀት ቢይዙም አብረው እየኖሩ መሆናቸውን እንዳረጋገጠ ገልጿል፡፡ ሥራም አብረው እየሠሩ መሆኑንም አክሏል፡፡ ሁሉንም ነገር በሰነድ እንደሚረጋግጥም ገልጿል፡፡ የግራ ቀኙን ክርክር የሰማው ፍርድ ቤቱ የምርመራ መዝገቡን በአዳር አስቅርቦ ካየ በኋላ፣ ማክሰኞ ታኅሳስ 2 ቀን 2011 ዓ.ም. የተጠርጣሪዎቹን መከራከሪያ ሐሳብ ውድቅ በማድረግ፣ መርማሪ ቡድኑ የጠየቀውን 14 ቀናት ለተጨማሪ ምርመራ ፈቅዷል፡፡ ሀብት እንደሌላቸው በመግለጽ መንግሥት ተከላካይ ጠበቃ እንዲያቆምላቸው የጠየቁትን በሚመለከት መርማሪ ቡድኑ፣ አቶ መአሾ በባንክ ከ400 ሺሕ ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ እንዳላቸውና አቶ ሀዱሽ በባንክ በባለቤታቸው ስም ካስቀመጡት 500 ሺሕ ብር ላይ ባለቤታቸው ሰሞኑን 50 ሺሕ ብር ብቻ አውጥተው፣ 450 ሺሕ ብር እንዳላቸው ማረጋገጡንና ከባንኮቹ ማረጋገጫ ሰነድ እንደሚያቀርብ አስረድቷል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ መርማሪ ቡድኑ ማረጋገጫውን ለታኅሳስ 8 ቀን 2011 ዓ.ም. እስከሚያቀርብ ቃለ መሃላው እንዳይፈጸም ትዕዛዝ ሰጥቶ፣ ክርክሩን ለታኅሳስ 16 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ በተመሳሳይ ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው ከጥቅምት 30 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በእስር ላይ የሚገኙትና በእነ አቶ ጎሃ አጽብሐ የምርመራ መዝገብ ተካተው እየተመረመሩ የሚገኙ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንና የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር 33 ተጠርጣሪዎች ማክሰኞ ታኅሳስ 2 ቀን 2011 ዓ.ም. ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን በተሰጠው 14 ቀናት ውስጥ  የሠራውን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ በተሰጠው ጊዜ የ21 ተጎጂዎችን የምስክርነት ቃል መቀበሉን፣ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ድብቅ እስር ቤት መኖሩን መለየቱን፣ ተጠርጣሪዎችን በተጎጂዎች ለማስለየት ያደረገው ጥረት ተጠርጣሪዎቹ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካለት እንደቀረ አስረድቷል፡፡ ከሁሉም ተቋማት ተጠርጣሪዎቹን የሚመለከቱ ሰነዶችን በደብዳቤ መጠየቁን፣ በግፍ የተገደሉ ዜጎች የአስከሬን ምርመራ ሰነድ ከዳግማዊ ምኒልክና ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታሎች መጠየቁን፣ ተጠርጣሪዎቹ ሲጠቀሙበት የነበሩትን የተለያዩ የምርመራ መዛግብትን ከየተቋማቱ መጠየቁንና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የታሰሩ ዜጎች ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መኖሩ የተረጋገጠባቸው የምርመራ ሰነዶችን መጠየቁን አስረድቷል፡፡መርማሪ ቡድኑ በቀጣይ በቅርብ የሚያገኛቸውንና ራሳቸው እየመጡ የምስክርነት ቃል የሚሰጡትን ተጎጂዎችና አካላቸው በመጉደሉ ወደ ተቋሙ መምጣት የማይችሉ፣ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ተጎጂዎችን የምስክርነት ቃል የሚቀበል የምርመራ ቡድን አቋቁሞ ሊልክ መሆኑን አስረድቷል፡፡ የሕክምና ማስረጃዎችን መሰብሰብ፣ በተጎጂዎች ንብረት ላይ የደረሰውን ጉዳት ለይቶ ማስገመት፣ በቂሊንጦ ማረፊያ ቤት ቃጠሎ ምክንያት ሸዋ ሮቢት ተወስደው በደረሰባቸው ከፍተኛ ድብደባ ጉዳት የደረሰባቸውን የምስክርነት ቃል መስማት እንደሚቀረው አስረድቶ፣ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ የተጠርጣሪዎች ጠበቆች በተለይ አቶ ጎሃ አጽብሐ፣ አቶ አማኑኤል ኪሮስ፣ አቶ ደርበው ደምመላሽ፣ አቶ ተስፋዬ ገብረ ፃዲቅና ሸዊት በላይ በሰጡት ምላሽ፣ ደንበኞቻቸው በሥውር እስር ቤት እንዲታሰሩ በማድረግ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዲፈጸም ትዕዛዝ ሰጥተዋል ተብለው መጠርጠራቸውን አስታውሰዋል፡፡ ነገር ግን ራሱ መርማሪ ቡድኑ በጥቅሉ ‹‹በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረዋል›› ከማለት ውጪ እያንዳንዱ ተጠርጣሪ በምን ወንጀል እንደተጠረጠረ እንደማያውቅ ተናግረዋል፡፡ ነገር ግን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 19(1) ላይ እንደተደነገገው አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር እንደዋለ፣ በምን እንደተጠረጠረ፣ በግልጽና በሚያውቀው ቋንቋ እንዲነገረው መደንገጉን አስረድተዋል፡፡ ደንበኞቻቸው ለ31 ቀናት የታሰሩ ቢሆንም፣ የተጠረጠሩበት ወንጀል እንዳልተነገራቸው አክለዋል፡፡ መርማሪ ቡድኑ ባለፈው ቀጠሮ የማስረጃ ሰነዶችን ለመሰብሰብ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቆ እንደተፈቀደለት አስታውሰው፣ ከ14 ቀናት ቆይታ በኋላ በድጋሚ ሰነድ ለመሰብሰብ 14 ቀናት የሚጠይቅ ከሆነ፣ ሥራ አለመሥራቱን እንደሚያመለክት በመግለጽ ተቃውመዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በአንድ ተቋም ውስጥ የሚሠሩ በመሆናቸው የሚፈለግባቸውን የሰነድ ማስረጃ በቀላሉ መሰብሰብ እንደሚችል ጠበቆቹ ተናግረው፣ ሆን ተብሎ በዋስ እንዳይወጡ የሚደረግ መሆኑንና ይኼም የሰብዓዊ መብት ጥሰት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አሥራ አንደኛ ተጠርጣሪ በቅርቡ ባላቸው ሥነ ምግባር የተነሳ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል መምርያ ምክትል ዳይሬክተር ተደርገው መሾማቸውን ጠቁመው፣ በሥርዓቱ ለስብሰባ ተጠርተው ከመታሰራቸው ውጪ ምንም የሚውቁትና የሠሩት ወንጀል እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ መረጃ የመሰብሰብና ተንትነው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥር ለተቋቋመው ብሔራዊ ምክር ቤት የሚያቀርቡ ባለሙያ መሆናቸውንም አክለዋል፡፡ መርማሪ ቡድኑ በማን ላይ ምን ያህል የምስክር ቃል እንደተቀበለና የተጠረጠሩበትን ወንጀል ለይቶ ማሳወቅና ለፍርድ ቤቱም ማቅረብ ሲገባው፣ ዝም ብሎ በጥቅል የ21 ምስክሮችን ቃል መቀበሉን ብቻ መግለጹ ተገቢ እንዳልሆነም ተናግረዋል፡፡ ምርመራው ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 19(4) ድንጋጌ አኳያ መታየት እንዳለበት ጠበቆቹ አሳስበው፣ የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብታቸው ከግምት ውስጥ መግባት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የምርመራ መዝገቡን አስቀርቦ ማየት እንዳበት ያሳሰቡት ጠበቆቹ፣ ምክንያታቸው ደግሞ መርማሪ ቡድኑ በጅምላ ‹‹በሰብዓዊ መብት ጥሰት›› እያለ በየቀጠሮው ተጨማሪ ጊዜ ከመጠየቅ ባለፈ፣ በደንበኞቻቸው ላይ ምንም ዓይነት ምርመራ የጀመረ ስላልመሰላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተለይ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ሠራኞች ከመሆናቸው አንፃር፣ ከቂሊንጦ ቃጠሎ ጋር የሚያገናኛቸው ነገር እንደሌለም ጠቁመዋል፡፡ መርማሪ ቡድኑ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ከማዋሉ በፊት፣ የምስክሮችን ቃል ሳይቀበልና ሰነዶችን ሳይሰበስብ እንዲታሰሩ ማድረግ ሕገ መንግሥቱንና ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎችን ጭምር መጣስ ስለሆነ፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጥያቄው ውድቅ ተደርጎ ከእስር እንዲፈቱም ጠይቀዋል፡፡ፍርድ ቤቱ ጥያቄያቸውን የሚያልፈው ቢሆን እንኳን፣ እያንዳንዳቸው ተጠርጣሪዎች የተጠረጠሩበት ወንጀል ተገልጾና መዝገቡ ተለይቶ እንዲቀርብ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ የተለያዩ ተቋማት ሠራተኞች በመሆናቸው የተጠረጠሩት ወንጀልም አንድ ሆኖ መቅረብ እንደሌለበት በማስረዳት፣ ተቃውሞአቸውን አቅርበዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ክርክራቸውን ሳይጨርሱ የፍርድ ቤቱ የሥራ ሰዓት በማብቃቱ፣ የቀሪዎቹን ተጠርጣሪዎች ክርክር ለመስማት ለረቡዕ ታኅሳስ 3 ቀን 2011 ዓ.ም. ፍርድ ቤቱ በአዳር ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡         ", "passage_id": "aace1705f3b7723c3ce2d05cf336e87a" }, { "passage": "በሶማሌ ክልል ከሐምሌ 26 እስከ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. ተፈጥሮ በነበረው  ሁከትና ብጥብጥ ምክንያት ከተፈጸመ ግድያ፣ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት፣ ዘርን መሠረት ያደረገ ጥቃትና ማፈናቀል፣ የሃይማኖት ተቋማት ቃጠሎና ንብረት ዘረፋ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው የታሰሩት አቶ ቴዎድሮስ አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ)፣ የክልሉ ፕሬዚዳንት ከነበሩት አቶ አብዲ መሐመድና ከሌሎች ባለሥልጣናት ጋር ግንኙነት እንደነበራቸው ለፍርድ ቤት ተነገረ፡፡የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ጥቅምት 23 ቀን 2011 ዓ.ም. ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ ወንጀል ችሎት እንዳስረዳው፣ ግለሰቡ በክልሉ ታዋቂ ባለሀብት ናቸው፡፡ እሳቸው በፌስቡክና በተለያዩ መንገዶች ባደረጉት ቅስቀሳ በክልሉ ተፈጥሮ የነበረው ሁከትና ብጥብጥ እንዲባባስ አድርገዋል፡፡ አሁን በእስር ላይ ከሚገኙት የቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንትና ሌሎች ባለሥልጣናት ጋርም ግንኙነት እንደነበራቸው፣ ማስረጃዎችን መሰብሰቡን መርማሪ ቡድኑ አስረድቷል፡፡ ባለሀብቱ አሁን በሥራ ላይ ከሚገኙ የቀድሞ ባለሥልጣናት ጋር ግንኙነት አላቸው ብሎ ስለሚያስብ ምስክሮችን ሊያባብሉ፣ ሊያስጠፉ፣ ሊያስፈራሩ፣ ሰነዶችንም ሊያጠፉ ስለሚችሉ የጠየቁትን ዋስትና እንደሚቃወም መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡በተጠርጣሪው ላይ በተሰጠው የ14 ተጨማሪ ቀናት የሦስት ምስክሮችን ቃል መቀበሉን፣ የእሳቸውን የተከሳሽነት ቃል መቀበሉን፣ የጣት አሻራ ለፎረንሲክ ምርመራ መስጠቱን፣ የወንጀል ድርጊት እንዲፈጸም ሲነጋገሩባቸው የነበሩ ሁለት ሞባይል ስልኮች ለቴክኒክ ምርመራ መስጠቱን፣ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ኮምፒዩተርና ላፕቶፕ ለምርመራ መስጠቱን፣ እሳቸው ባነሳሱት ሁከትና ብጥብጥ የሞቱ በርካታ ሰዎች በጅምላ ከተቀበሩበት አስከሬናቸው ወጥቶ እንዲመረመር ሰጥቶ ውጤት እየተጠባበቀ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ግብረ አበሮቻቸውን መያዝ፣ የቀሩ ምስክሮችን ቃል መቀበል፣ የአስከሬን ምርመራ ውጤት መቀበል፣ የተጎጂዎችን ምርመራ ውጤት መቀበል፣ ከክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ወጪ ከተደረገው ገንዘብ እሳቸውም ተቋዳሽ በመሆናቸው ወጪ የተደረገበትን ሰነድ ማስተርጎም ስለሚቀረው፣ ተጨማሪ የ14 ቀናት ጊዜ እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡አቶ ቴዎድሮስ በጠበቃቸው አቶ ዳግም ተሾመ አማካይነት ባቀረቡት መቃወሚያ፣ ደንበኛቸው የተጠረጠሩበት ጉዳይ ግልጽ እንዳልሆነላቸው ተናግረዋል፡፡ ደንበኛቸው ከአስከሬን ምርመራ ጋር ምን እንዳገናኛቸው እንዳልገባቸው አክለዋል፡፡ አቶ ቴዎድሮስ ከታሰሩ አንድ ወር እንዳለፋቸውና በጅግጅጋ ቃላቸውን እንደሰጡም ተናግረዋል፡፡ ግብረ አበሮችን መያዝ የፖሊስ ሥራ በመሆኑ ደንበኛቸውን በማቆያ ቤት የሚያስቆይ አለመሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ከሰነድ ማስተርጎም ጋርም ምንም ግንኙነት እንደሌለውና የኮምፒዩተራቸውንና የላፕቶፓቸውን የይለፍ ቃል ስለሰጡ፣ 14 ተጨማሪ ቀናት ለመጠየቅ የሚያስፈልግ ነገር እንደሌለና ተገቢ አለመሆኑም አስረድተዋል፡፡ ደንበኛቸው በክልሉ ባላቸው ድርጅት ውስጥ የሚሠሩ ሠራተኞች ወደ ሥራ እንዳይገቡ በፖሊስ መከልከላቸውን ጠቁመው፣ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸውና የዋስትና መብታቸውንም እንዲጠብቅላቸው ጠይቀዋል፡፡ መርማሪ ፖሊስ ዋስትናውን እንደሚቃወም ከላይ መጥቀሱን አስታውሶ፣ በጅግጅጋ ስለመታሰራቸውና ቃላቸውን ስለመስጠታቸው የሚያውቀው እንደሌለ በማስረዳት፣ የጠየቀው ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ፣ መርማሪ ቡድኑ በተሰጠው ጊዜ ሰፊ ሥራ መሥራቱን መገንዘቡን አስታውቆ፣ ለቀሪ ምርመራ የጠየቀው ጊዜ ተገቢ መሆኑን ስላመነበት የጠየቀውን 14 ቀናት በመፍቀድ የተጠርጣሪውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል፡፡ ለኅዳር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡    ", "passage_id": "47a657f5641eb2eaac6b456f982d3271" }, { "passage": "በሰሜን ዕዝ ላይ ከተፈጸመው ጥቃትና ከተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉ፣ የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖችና የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች፣ ከኅዳር 23 እስከ 25 ቀን 2013 ዓ.ም. ባሉት ቀናት ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች፣ የመከላከያ መገናኛ ሬዲዮና ኔትወርክ ዘርፍ ሠራተኞች የነበሩ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የዲጂታል ወያኔ (DW) ሚዲያ ጋዜጠኞችና ቀደም ብሎ የአውራምባ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረውና በአውራምባ ታይምስ ኦንላይን አዘጋጅ፣ እንዲሁም በተለያዩ የንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች ናቸው፡፡ የመከላከያ ሬዲዮ፣ መገናኛና ኔትወርክ ዘርፍ ሠራተኛ እንደነበሩት የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን የገለጻቸው ተጠርጣሪዎች፣ ብርጋዴር ጄኔራል አብርሃ መውጫ፣ ኮሎኔል ገብረ ሕይወት ደስታ፣ ኮሎኔል ዮሐንስ በቀለ፣ ኮሌኔል ዘነበ ታመነና ሻለቃ ገብረ እግዚአብሔር ግርማዬ ናቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ለመከላከያ ሠራዊቱ መጠቀሚያ የተዘረጋን የግንኙነት ኔትወርክ ለሌላ ተልዕኮ በማዘጋጀት፣ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን የሚያሳይ ማስረጃ ማግኘቱን፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ምክንያቶች ሁከትና ግጭቶች ሲፈጠሩ፣ ግጭቱን ማስቆም ወይም የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንዳይቻል የሬዲዮ መገናኛውን የማቋረጥ ሥራ ይሠሩ እንደነበር፣ ለመከላከያ ሠራዊቱ የተገዛን መሣሪያ ለፀረ ሰላም ኃይሎች ሲያስታጥቁ እንደነበር የሚያሳይ ማስረጃ ማግኘቱን፣ ከተፈቀደላቸው ውጪ የጦር መሣሪያ በቤታቸው በተደረገ ብርበራ መገኘቱንና ከወታደራዊ ባህሪ ባፈነገጠ ሁኔታ፣ ከመስከረም 30 በኋላ ‹‹መንግሥት የለም›› በማለት የሠራዊት አባላትን ለብጥብጥ ሲያነሳሱና ሲያስተባብሩ እንደነበር የሚያሳዩ መረጃዎችን ማግኘቱን፣ መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡በተጠርጣሪዎቹ ላይ የምስክሮችን ቃል መቀበሉንና ሰፊ ሥራ መሠራቱን አስረድቶ፣ በተጠርጣሪዎቹ ምክንያት በአገር መሠረተ ልማቶች ላይ የደረሰን ጉዳት፣ በንብረት ላይ የደረሰን ጉዳት፣ በሰዎች ሕይወትና አካል ላይ የደረሰውን ጉዳት ለማጣራትና ተጨማሪ በርካታ ምርመራዎችን ለመሥራት ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡ መከራከሪያ ሐሳብ እንደገለጹት፣ መርማሪ ቡድኑ እንደገለጸው የመከላከያ ሬዴዮ መገናኛ ዘርፍ ሠራተኞች ናቸው፡፡ ነገር ግን በተገለጸው የወንጀል ድርጊት ውስጥ አልተሳተፉም፡፡ በመሆኑም የዋስ መብታቸው ተከብሮላቸው በውጪ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ፣ የተጠርጣሪዎቹን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ለመርማሪ ቡድኑ 12 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ፈቅዷል፡፡ ፍርድ ቤት የቀረቡት የዲጂታል ወያኔ (DW) ሚዲያ ጋዜጠኞች ሀብቱ ገብረ እግዚአብሔር፣ አብርሃ ሐጎስ፣ ፀጋዬ ሐጎስና ካሳ ማቴዎስን ጨምሮ አሥር ተጠርጣሪዎች ሲሆኑ፣ መርማሪ ቡድኑ እንዳስረዳው፣ ተጠርጣሪዎቹ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ሲንቀሳቀሱና ሐሰተኛ ማስረጃ ሲያሠራጩ እንደነበር አስረድቷል፡፡ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አራት ተጠርጣሪዎች የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ስለተገኘባቸው አለመቅረባቸውንም መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ አስታውቆ፣ የምስክሮች ቃል መቀበሉንና የተለያዩ የሰነድ ማስረጃዎችን መሰብሰቡን ገልጿል፡፡ ከሞባይሎቻቸውና ኢሜይላቸው የተለያዩ ማስረጃዎችን ማግኘቱን ጠቁሞ፣ ሌሎች ማስረጃዎችን ለመሰብሰብና ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ 14 ቀናት ጠይቋል፡፡ተጠርጣሪዎቹ ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ፣ መርማሪ ቡድኑ የወንጀል ተሳትፎውን በጥቅል ማቅረቡ ተገቢ ባለመሆኑ፣ የእያንዳንዳቸው የወንጀል ተሳትፎ ተለይቶ እንዲቀርብላቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል፡፡ በውጪ ሆነው እንዲከታተሉም እንዲፈቀድላቸው አመልክተዋል፡፡ፍርድ ቤቱ የመርማሪ ቡድኑን የምርመራ ሪፖርትና የተጠርጣሪዎቹን አቤቱታ ከሰማ በኋላ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ በዚህም መርማሪ ቡድኑ በተሰጠው ጊዜ መሥራት የሚገባውን ያህል ሠርቷል ብሎ እንደማያምን በመግለጽ፣ ተጠርጣሪዎቹ የተወሰኑት በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውንና የኑሮ ሁኔታ በማገናዘብ እያንዳንዳቸው በአሥር ሺሕ ብር ዋስ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡ ነገር ግን በፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ቅር የተሰኘው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ይግባኝ ጠይቆ የሥር ፍርድ ቤት ትዕዛዝን ማሳገዱን ሪፖርተር ለማረጋገጥ ችሏል፡፡ በሌላ የምርመራ መዝገብ ፍርድ ቤት የቀረበው ቀደም ብሎ ኅትመት ላይ የነበረው አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የአውራምባ ታይምስ ኦንላይን አዘጋጅ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ነው፡፡ ጋዜጠኛ ዳዊትን በሚመለከት የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዳው፣ ተጠርጣሪው የተዛባ መረጃ በማሠራጨት ግጭት በመቀስቀስ ወንጀል ተጠርጥሮ ምርመራ እያደረገበት መሆኑን በማሳወቅ 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱም አንድ ቀን በመቀነስ 13 የምርመራ ቀናትን ፈቅዷል፡፡ ቤቱ ሲበረበር 35 መትረየስ ሽጉጦች፣ አንድ ኮልት ሽጉጥና ሌሎች መሣሪያዎች አስቀምጦ መገኘቱን መርማሪ ቡድኑ የገለጸው አቶ ደፋር ተሰማ የተባለ ተጠርጣሪም ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡ እንደ መርማሪ ቡድኑ ሪፖርት ተጠርጣሪው ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ በማሰብ፣ ከፀረ ሰላም ኃይሎች ተልዕኮ ተቀብሎ፣ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በተፈጸመበት ዕለትና በተመሳሳይ ጊዜ፣ በኦሮሚያ አካባቢ ጥቃት ሊፈጽም ሲንቀሳቀስ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡ የተለያዩ ምርመራዎችን እያደረገ መሆኑን ገልጾ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪው ለፍርድ ቤት እንደገለጸው፣ የተጠቀሰውን መሣሪያ ሌላ ሰው በእሱ ቤት አስቀምጦት ካልሆነ በስተቀር፣ እሱ እንዳላስቀመጠ ተናግሯል፡፡ የዋስትና መብቱ እንዲከበርለትም ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ለመርማሪ ቡድኑ ዘጠኝ ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዶ ለታኅሳስ 2 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ የሕወሓት ቡድን በሚያደርግላቸው የገንዘብ ድጋፍ በማኅበራዊ ድረ ገጾች ግጭት ቀስቃሽ መረጃዎችን በማሠራጨት የተጠረጠሩ ሦስት ተጠርጣሪዎችንም መርማሪ ቡድኑ ፍርድ ቤት አቅርቦ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጠይቆባቸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹም ቢኒያም ተመስገን፣ ሥዩም ገብረሚካኤልና አሉላ ኢሳያስ የሚባሉ መሆናቸውን ጠቁሞ፣ የምስክሮች ቃል መቀበሉንና ሞባይሎቻቸውንና ኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን ለምርመራ መላኩን ለፍርድ ቤቱ ገልጿል፡፡ ለተጨማሪ ምርመራም 14 ቀናት ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በጠበቃ ታግዘው አቶ ቢኒያም ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ እንደተናገሩት፣ መኪና አስመጪ እንጂ ከሕወሓት ቡድን ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡ ለፖሊስ አጋዥ ሆነው እንደሚሠሩ ጠቁመው፣ ላለፉት 27 ዓመታት ከቡድኑ ጉዳትና መጎሳቆል የደረሰባቸው እንጂ፣ ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌላቸው በድጋሚ በመግለጽ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ክርክሩን ከሰማ በኋላ ለመርማሪ ቡድኑ ስምንት ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ፈቅዷል፡፡ አብዱል ሰላም አብዱልአዚዝ በተባለ ተጠርጣሪ የምርመራ መዝገብ የተካተቱ አራት ተጠርጣሪዎችም ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን፣ ከሕወሓት ቡድን ተልዕኮ በመቀበል ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ የተለያዩ የጦር መሣሪያዎቸን ይዘው መገኘታቸውንና በመሣሪያው ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑንም አክሏል፡፡ የምስክሮችን ቃል መቀበሉን ጠቁሞ፣ ግብረ አበሮችን ለመያዝ ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጾ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹም መርማሪ ፖሊስ ከገለጸው የወንጀል ድርጊት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌላቸው በመግለጽ፣ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸውና በውጪ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ጠይቀዋል፡፡መርማሪ ቡድኑ በድጋሚ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው መከራከሪያ፣ ተጠርጣሪዎቹ በተደጋጋሚ መቀሌ በመመላለስ የሽብር ተግባር ለመፈጸም ሥልጠና መውሰዳቸውንና የአገሪቱን መሠረተ ልማት ለማውደም ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን በማስረዳት፣ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድት ጠይቋል፡፡ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ ዘጠኝ ቀናት ፈቅዷል፡፡ ተስፋዬ ተረፈ፣ አበበ መረሳና ሃምሳ አለቃ ሕይወት በርሄ የተባሉ ተጠርጣሪዎችም ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን፣ ፖሊስ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ከኦነግ ሸኔና ከሕወሓት ቡድን ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ሀፍቱ ካሰው፣ ተስፋዬ ተረፈና አበበ መርሳ በጠበቃ እንዲወከሉ በመጠየቃቸው የእነሱን አቆይቶ ሃምሳ አለቃ ሕይወት ላይ መርማሪ ቡድኑ የጠየቀውን 14 ቀናት ፈቅዷል፡፡   ", "passage_id": "d4fa5c3a0e777db5cb96d29285f59bed" } ]
928713b70f0ae1ed2748f15cab6354b5
5e4d2ef8b38ea306d8d624c93f991a5a
ከመተከል ዞን ቡለን ወረዳ የተፈናቀሉ ወገኖች ለረሃብ አደጋ መጋለጣቸውን ተናገሩ
መሀመድ ሁሴንአዲስ አበባ፡- በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በሚገኙ ቀበሌዎች በንፁሃን ላይ ከተፈፀመው ጥቃት አምልጠው በቡለን ከተማ የተጠለሉ ተፈናቃዮች በረሃብና በጥም የተነሳ ለሞት አደጋ መጋለጣቸውን ተናገሩ፡፡አስተያየታቸውን ትናንት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ የሰጡት እነዚሁ ተፈናቃዮች፤ ከግድያው ለማምለጥ ምንም ነገር ሳይዙ ከቤታቸው በመውጣታቸው የተነሳ አሁን ላይ የሚበሉትና የሚጠጡት እንዳጡና ከመንግሥትም ያገኙት ድጋፍ እንደሌለ በምሬት ተናግረዋል።የስምንት ልጆች አባት የሆኑትና በበኩጂ ቀበሌ ከአስር ዓመታት በላይ የኖሩት አርሶ አደር ደረጀ በየነ እንደገለፁት፤ ከሞት አምልጠውና ከአርባ አምስት ኪሎ ሜትር በላይ በእግራቸው ተጉዘው ቡለን ወረዳ መድረስ ቢችሉም፣ በርሃብና በጥም የተነሳ ሌላ ሞት እንደተጋፈጡና ጠያቂ የመንግሥት አካል እስካሁን አላገኙም። በወረዳው ሥር የሚገኙ ሁሉም የቀበሌ ነዋሪዎች የእግር መርገጫ እስኪጠፋ ድረስ በቡለን ወረዳ ተሰባስበው በረሃብ እየተቆሉ ይገኛሉ ያሉት አርሶ አደር ደረጀ፤ ‹‹ህይወታቸውን ካጡት እህት ወንድሞቻችን ሐዘንና ድንጋጤ ሳንወጣ ይዘን የሸሸናቸውን ልጆቻችንን ልናጣ የምንችልበት አደገኛ የረሃብ ችግር ውስጥ ወድቀናል፡፡ ጠያቂ አካል አላገኘንም፡፡ ትምህርት ቤቶች እና አዳራሾች በተፈናቃዮች ሞልተው ተጨናንቀዋል፡፡ ህፃናት ልጆቻችን የሚልሱት የሚቀምሱት አጥተዋል፡፡ በዚህ የተነሳም በከፍተኛ ጭንቀት ላይ እንገኛለን›› ሲሉ ሀሳባቸውን በምሬት ገልፀዋል፡፡ ‹‹በፍራቻና በሥጋት ሰቀቀን ውስጥ መኖር ከጀመርን ዓመት አልፎናል፡፡ ከወረዳና ከክልል የሚመጡ አመራሮች የጉሙዝ ማህበረሰብን ብቻ ለይተው ይሰበስባሉ፡፡ ለእኛ ዞረው ሰላም ነው፤ ምንም ችግር አይደርስባችሁም እያሉ ሲያዘናጉን ኖረዋል፡፡ ስለዚህ ከጀርባ ሌላ የጭፍጨፋ ሴራ እየተዘጋጀ ሕዝቡ እንዳይነቃ እና ወደሌላ አካባቢ እንዳይሸሽ ሲደረግ ኖሯል፡፡ በዚህ የተነሳም ከበኩጂ ብቻ ያለቀው ሰው ብዙ ነው፡፡ እኔ በዓይኔ ተሰብስቦ የተመለከትኩት 207 አስከሬን ነው” ያሉት አርሶ አደር ደረጀ፤ የወንድማቸው አምስት ልጆችና ባልና ሚስትን ጨምሮ ሰባት ቤተሰባቸው እንደተገደሉባቸው በሐዘን ተናግረዋል፡፡ የጭላንቆ ቀበሌ ነዋሪው የሆኑት ሌላው አስተያየት ሰጪ አርሶ አደር ወንድማገኝ ሻምበል በበኩላቸው፤ የተፈፀመው ዘግናኝ ጭፍጨፋ አስከፊ ከመሆኑም በላይ በህይወት የተረፍነውም ለከፍተኛ መከራ ዳርጎናል ብለዋል፡፡ “ህፃናት እና ሴቶች ከጭፍጨፋው አምልጠው በቡለን ወረዳ በመሰባሰብ በከፍተኛ ረሃብ ላይ ወድቀዋል፡፡ ማንም የሚጠይቅ አካል የለም፡፡ በዚህ የተነሳ ከፍተኛ ተጨማሪ እልቂት መፈጠሩ አይቀርም” ሲሉ አርሶአደሩ ሥጋታቸውን አስረድተዋል፡፡አመራሩ የችግሩ ዋና አካል መሆኑን ያነሱት አርሶ አደር ወንድም አገኝ ፤ ‹‹ከወረዳ ወደ ቀበሌ የሚመጡ አመራሮች እኛን ሊያስገድሉን ነበር፡፡ ከጭላንቆ ቀበሌ ሩጠን በማምለጥ ከምሽቱ ሦስት ሰዓት አዲስ ዓለም ከምትባል ቀበሌ ገብተን ተቀመጡ መከላከያ ሠራዊት መጥቶላችኋል ብለው አታለሉን። በዚህም የተነሳ ወንድማችን በአራት ቀስት ተመትቶ ሞቷል›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ሕብረተሰቡ አብሮ ከጉምዝ ብሔረሰቦች ጋር ቡና የሚጠጣ ሕዝብ ነው ያሉት አርሶ አደሩ፤ “ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እኛ ወደ ማሣ ሥራ ስንሄድ ከወረዳ ከሚመጡ አመራሮች ጋር ብቻቸውን ይመክራሉ፤ በዚህም የተነሳ ጥቃቱ እየጨመረ መጥቷል›› ብለዋል፡፡“ብዙ ወገኖቻችንን በግድያው ከማጣታችን በላይ በመከራ ላይ መከራ፣ በችግር ላይ ችግር እያሰቃየን እንገኛለን፡፡ የሦስት ቀን አራስ ህፃን ልጅ በዘንቢል ይዘን ነው የወጣነው፡፡ አዝመራዬን ወቅቼ 180 ኩንታል ሜዳ ላይ እንደደረደርኩት ትቼው ወጥቻለሁ፡፡ መኪና እንኳን ማግኘት አልቻልንም፡፡ አምልጠን የወጣነውም በእግራችን ነው፡፡ ባዶ ራቁታችንን ወጥተን ቡለን ብንደርስም ሌላ መከራ ነው የጠበቀን፡፡ ወድቀን ያለነው ከሕብረተሰቡ ላይ ነው፡፡ እኔ አመራር ነኝ ብሎ ተፈናቃዮችን ያነጋገረና የጠየቀ አካል እስካሁን የለም›› በማለት ብሶታቸውን ተናግረዋል፡፡ በጉሙዝ ማህበረሰብ እና በሌላው ሕብረተሰብ መካከል ምንም አይነት ችግር እንደሌለ የገለፁት አስተያየት ሰጪዎቹ፤ “የሚያስፈጁን በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ኃላፊነት የተሰጣቸው አመራሮች እኩይ ድርጊት በመሆኑ አጥርቶ እርምጃ መውሰድ እና የተፈናቀለውን ማቋቋም አስፈላጊ ነው” ሲሉ መፍትሄ ያሉትን ጠቁመዋል፡፡ እንደ ዝግጅት ክፍል የነዋሪዎቹን አስተያየት በመያዝ ወደሚመለከታቸው የቤንሻንጉል ክልል የሥራ ኃላፊዎች በመደወል ጉዳዩን ለማጣራትና አስተያየታቸውን እንዲሰጡን ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ ሆኖም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ለኢቢሲ በሰጡት አስተያየት፤ በግድያው እጃቸው አለበት ተብለው የሚጠረጠሩት አመራርም ይሁን፣ ግለሰቦችም ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ እርምጃ እየወሰዱ መሆናቸውን አስታውቀዋል።“አሁንም ቢሆን በህብረተሰቡ በተለያዩ አጋጣሚዎች በተደጋጋሚ በግጭቱ ላይ የአመራሮች ተሳትፎ አለበት የሚል ነገር አለ፡፡ እኛ ዝግ አላደረግነውም፤ እንደክልል መንግሥት የሚወራው ወሬ እንደተጠበቀ ሆኖ የማጥራት ሥራዎች በመሥራት ተጨባጭ ማስረጃዎች ስናገኝ ማንኛውም ሰው ወደ ሕግ እንዲቀርብ እያደረግን ነው ያለነው” ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38147
[ { "passage": "ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ ካማሽ ዞን፣ ያሶ ወረዳ ከሚገኘው ቀያቸው ተፈናቅለው ባህርዳር ከተማ የገቡ አምስት መቶ ተፈናቃዮች ከክልሉ መንግሥት ድጋፍ አለማግኘታቸውን ገልፀው ቅሬታ አቀረቡ።ተፈናቃዮቹን ወደ ትውልድ ቦታቸው ለማመላለስ የትራንስፖርት አገልግሎት ቢያቀርብም ተፈናቃዮቹ ለመሄድ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል ሲል የክልሉ መንግሥት ምላሽ ሰጥቷል።", "passage_id": "8abed95bbddafe1b1bad60801c94f5e6" }, { "passage": "በሁለቱ አካባቢዎች ከሳምንት በፊት በተከሰተውና ለቀናት በቆየው ግጭት ከተፈናቀሉት ነዋሪዎች በተጨማሪ በርካታ ሰዎች መሞታቸው የተገለጸ ሲሆን በንብረትም ላይ ከፍተኛ ውድመት መድረሱን ነዋሪዎች ተናግረዋል። \n\nበአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ገብረ ጻዲቅ በተከሰተው ችግር ምክንያት በዞኑ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ41 ሺህ በላይ እንደሆኑ ለቢቢሲ ገልጸዋል።\n\nበግጭቱ ምን ያህል ሰዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ የተጠየቁት ኃላፊው \"የሞቱ ሰዎች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ የሚያጣራ ቡድን አዋቅረን መረጃ እየተሰበሰበ ነው\" ብለዋል።\n\nእስካሁን ድረስ እጃቸው ላይ የደረሰው መረጃ 41 ሺህ 625 ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን የሚያሳይ መሆኑን የገልጹት አቶ ታደሰ፤ ነገር ግን ወደ ዘመድ አዝማድ እና ሌላ አካባቢ የሸሹ ስለሚኖሩ ቁጥሩ ከዚህም በላይ ሊሆን ይችላል ሲሉ ይናገራሉ።\n\nበሌላ በኩል ደግሞ ግጭቱ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ውስጥ የምትገኘዋ ጅሌ ድሙጋ አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ጀማል ሐሰን በተፈጠረው ችግር ሳቢያ በወረዳቸው 40ሺህ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።\n\n\"እስካሁን እጃችን በደረሰው መረጃ መሰረት 67 ሰዎች መሞታቸውን፣ 114 መቁሰላቸውን እና በወረዳው ስምንት ቀበሌዎች 815 ቤቶች መቃጠላቸውን ለማወቅ ችለናል\" ሲሉ የደረሰውን ጉዳት በአሃዝ አስቀምጠዋል። \n\nከዚህ ቀደም ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወደ ሆስፒታል ሲሄዱ ጥቃት ደርሶባቸው ስለነበር አብዛኞቹ ተጎጂዎች በቤታቸው ውስጥ መቅረታቸውን እና በቂ ሕክምና አለማግኘታቸውንም ጨምረው አስረድተዋል። \n\nበጅሌ ድሙጋ ተፈናቅለው የሚገኙ ሰዎች ስላሉበት ሁኔታ የተጠየቁት አቶ ጀማል፣ እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት የተደረገላቸው ድጋፍ እንደሌለ እና የተፈናቀለው ገበሬ እርስ በእርስ እየተረዳዳ እንደሚገኝ ተናግረዋል።\n\nአክለውም የክልልም ሆነ የፌደራል አካላት ስለ አሉበት ሁኔታ ለመጠየቅ አለመምጣታቸውን ገልፀዋል።\n\nበግጭቱ የተፈናቀሉት ሰዎች ትምህርት ቤቶች መስጂዶች እና በተለያዩ ቦታዎች ተበተትነው እንደሚገኙ አቶ ጀማል ይናገራሉ።\n\nየሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪውአቶ ታደሰ በበኩላቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ደብረብርሃን፣ አጣዬ፣ ኤፍራታ፣ ሸዋ ሮቢት ገንደ ውሃ፣ መሀል ሜዳ እና የተለያዩ ቦታዎች እንደሚገኙ ተናግረዋል።\n\nአቶ ታደሰ አክለውም ግጭቱ ከተከሰተ በኋላ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ በማዋቀር የተፈናቀሉ ሰዎች እርዳታ እንዲያገኙ እየሰራን ነው ይላሉ።\n\n\"ሸዋ ሮበት አጣዬ እና ኤፍራታ ከተሞች ውስጥ የምግብ ቁሳቁስ ከማቅረብ ጀምሮ ለተጎዱ ሰዎች እርዳታ የማድረግ እንዲሁም ፀጥታውን የማስከበር ሥራዎችን እየሰራን ነው\" ብለዋል።\n\nአቶ ታደሰ አክለውም የፀጥታ ሁኔታውነ በማስመልከት በአጣዬ፣ በማጀቴ፣ እና በድሙጋ አልፎ አልፎ የተኩስ ድምጽ እንደሚሰማ እና ይህም ሕብረተሰቡን ስጋት ውስጥ መክተቱን ይናገራሉ።\n\nአቶ ጀማልም የአቶ ታደሰን ሃሳብ አረጋግጠው የመከላከያ ሠራዊት ተኩስ ወደ ሚሰማባቸው አካባቢዎች በመንቀሳቀስ ቁጥጥር እንደሚያደርግ ተናግረዋል።\n\nሕብረተሰቡ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ይፈልጋል የሚሉት አቶ ታደሰ ለዚህም ውይይትና መስማማት እንደሚያስልግ ተናግረዋል።\n\nየክልሉ መንግሥት አንድ ቡድን መላኩን ዞኑም ኮሚቴ ማዋቀሩን በመግለጽ እነዚህ ቡድኖች ግጭቱ ከተከሰተባቸው ሁለቱ ዞኖች ጋር በመሆን ችግሩን ይፈታሉ ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።\n\nበግጭቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ትራንስፖርት ወደ ሥራ ተመልሷል።\n\n ", "passage_id": "84faf2b8a4d152f46dc9615d58387751" }, { "passage": "ከደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ በማንነታቸው ምክንያት ጥቃት ደርሶባቸው ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውን የሚናገሩ በትምሕርት ቤት ውስጥ ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮች፤ ከጥቃት ነፃ ስለመሆናቸው ዋስትና እንደሌላቸው ገለፁ።በጥቃቱ የተገደሉ ሰዎች ቁጥርም 41 እንጂ መንግሥት እንዳለው 31 አለመሆናቸውን ተናግረዋል። የተፈናቃዮቹም ቁጥር 7 ሺሕ እንደሚደርስ ተናግረዋል።የደቡብ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ፤ ለደረሰው ጥቃት ተጠርጣሪ ናቸው ያላቸውን 54 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልፆ፤ የተገደሉ ሰዎች ደግሞ 31 መሆናቸው በሁለም የፀጥታ አካላት የተጣራ መሆኑን አስታውቋል።“ታጥቀው አከባቢውን ያተራምሱ ነበሩ» የተባሉ ሁለት ሽፍቶችም መገደላቸውን ተናግረዋል።\n", "passage_id": "36150f45b3b3c2b11a968ec37f59ebcc" }, { "passage": "በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ራንች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች የመድኃኒት ድጋፍ እንዲቀርብ ጠየቁ፡፡ባሕር ዳር፡ ታኅሥሥ 21/2013 ዓ.ም (አብመድ) ከመተከል ዞን ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ራንች መጠለያ ጣቢያ የሰፈሩ ተፈናቃዮች ከመንግሥት የጤና ተቋማት የማያገኙትን መድኃኒት በግል ገዝተው ለመጠቀም ባለመቻላቸው መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡ወይዘሮ ጦቢያው ጓንጉል ከመተከል ዞን ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ራንች በተባለ ጊዜያዊ መጠለያ ይገኛሉ፡፡ ወይዘሮ ጦቢያው የስኳር ህመም ታማሚ በመሆናቸው ወደ ጤና ጣቢያ ሄደው በነፃ ሙሉ የምርመራ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ምርመራውን አጠናቀው እንደወጡ መድኃኒት በጤና ተቋም ማግኘት ባለመቻላቸው ከግል ገዝተው እንዳይጠቀሙ የተፈናቀሉት ባዶ እጃቸውን በመሆኑ በሐኪም የታዘዘላቸውን መድኃኒት አለመውሰዳቸው ለጤና ችግር መዳረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ወይዘሮ ጦቢያው በመጠለያ ጣቢያው የመድኃኒት አቅርቦት አለመኖሩ ሞት እዚህም ተከትሎአቸው እንደመጣ ያህል እየተሰማቸው ነው። በመንግሥት የጤና ተቋማት ከምርመራ አገልግሎት በተጨማሪ መድኃኒት ሊቀርብላቸው እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡የተፈናቃዮች የጤና ኮሚቴ ሆነው በጊዜያዊነት በተቋቋመው መጠለያ በመሥራት ላይ የሚገኙት አቶ መለሰ ደሳለው ለተፈናቃዮች ጤና ትኩረት እየተሰጠ አለመሆኑን ነግረውናል። በሚኖሩበት አካባቢ በቂ መጸዳጃ፣ መጠለያ፣ ምግብ እና ውሃ የሌለ በመሆኑ የጤና ችግር እየገጠማቸው እንደሚገኝም ተናግረዋል።ከ50 ሰው በላይ በአንድ ድንኳን እንደሚገኝ የገለጹት አቶ መለሰ                                                                        ይህም ለተላላፊ በሽታዎች እንዳይጋለጡ ስጋት እንደፈጠረባቸው                                                                          ገልጸዋል።                                                                      መንግሥት ሁኔታዎች ተለውጠው ወደ ቀዬአቸው እስኪመለሱ                                                                           ትኩረት በመስጠት አስፈላጊ የህክምና እና የመድኃኒት ድጋፍ                                                                             እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ያነጋገርናቸው ሐኪም መኮንን ምናየሁ (ዶክተር) ዜጎች ከሚደርስባቸው ግድያ ለመሸሽ ከቀያቸው ሲፈናቀሉ በቅድሚያ ምግብ፣ ውሃ፣ መጠለያ፣ መጸዳጃ እና የህክምና አገልግሎት በፍጥነት ካላገኙ ለተለያዩ የጤና እክሎች ይዳረጋሉ ብለዋል፡፡ ኮሌራ፣ተቅማጥ፣ ወባ፣ ኮሮና ወረርሽኝ፣ የስኳር በሽታ፣ የደም ግፊት፣ ሳንባ ነቀርሳ፣ ድብርት እና ሌሎችም የተፈናቃዮች ስጋት ናቸዉ ብለዋል።መንግሥት እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የምግብ፣ የውሃ፣ የመጸዳጃ ቤት እና የጤና አቅርቦት ቅድሚያ ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል። ተፈናቃዮች በተጨናነቀ መጠለያ መኖራቸውን የተመለከቱት ዶክተር መኮንን መንግሥት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማቅረብ እና እንዲሁም የአስቸኳይ ጊዜ የህክምና ቡድን ማቋቋም እንደሚገባው ተናግረዋል።የቻግኒ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አቶ ያሬድ ስማቸው ዜጎች ከመተከል ዞን ተፈናቅለው ከመጡበት ቀን ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ጤና ጣቢያዎች እና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከጤና መምሪያ፣ ከጤና ቢሮ እና ከጤና ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡በቅርቡ ደግሞ የድንገተኛ አደጋ መከላከል እና መቆጣጠር ባለሙያ ተመድቦ ነፍሰጡር፣ የሚያጠቡ እናቶችን እና የምግብ እጥረት ያለባቸውን ሕጻናት የተለየ ድጋፍ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ኀላፊው አስታውቀዋል። ተከታታይ መድኃኒት የሚወስዱ፣ መድኃኒት ጀምረው ያቋረጡ ተፈናቃዮች ለተጨማሪ ህመም እንዳይጋለጡ የወረዳው ጤና ጥበቃ እየሠራ ነው ብለዋል።ለ927 ተፈናቃዮች እስከ አሁን የህክምና አግልግሎት መስጠታቸውን የተናገሩት አቶ ያሬድ የሆስፒታል እና የጤና ጣቢያ ባለሙያዎች ተናበው እንዲሰሩ መደረጉንም አስረድተዋል።ከጤና ሚኒስቴር እና ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመሆን ተንቀሳቃሽ ክሊኒክ ተቋቋሞ ተፈናቃዮች ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲታከሙ እየተመቻቸ እንደሆነም ነግረውናል፡፡ከብሔረሰብ አስተዳደሩ አንድ አምቡላንስ ለተፈናቃዮች ብቻ በመመደብ አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ለሚፈልጉት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ኀላፊው ተናግረዋል፡፡ተፈናቃዮች ከሆስፒታል ያላገኙትን መድኃኒት ከጤና ጣቢያ እንዲያገኙ ይደረጋል ያሉት የጤና ጥበቃ ጽሕፈት ኀላፊው በአሁኑ ወቅት በቂ የመድኃኒት አቅርቦት ባለመኖሩ ለተፈናቃይ ታማሚዎች በቂ መድኃኒት ማቅረብ አልተቻለም ብለዋል። የክልሉ ጤና ቢሮም ክትትል የሚያደርጉ ባለሙያዎችን ወደ ሥፍራው እንደተላከ ታውቋል።", "passage_id": "2d007405930552709e5fc60ed16f11ef" }, { "passage": "በደቡብ ክልል ሰሞኑን የጣለው ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍና ናዳ ከ6000 በላይ ዜጎችን ለአስቸኳይ የሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸው የክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስተወቀ። \nየክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ አበራ ዊላ ለተፈጥሮ አደጋው መከሰት መነሻው የተፈጥሮ ኃብት አያያዝ ጉድለት መሆኑን ጠቅሰው፣ የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ አለመኖር ችግሩን አባብሷል ብለዋል። \n", "passage_id": "605e65de51f2fd51ab9c26f6b0de878a" } ]
703dc9d35d45801b260a4826850e0270
1f35ffd690294983599ae0360f1b225b
ኢትዮጵያውያን አንድነታቸውን በማጠናከር የሚገጥሟቸውን ፈተናዎች በጋራ መክተው ማለፍ ይገባቸዋል ተባለ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ከመቼውም ጊዜ በላይ ዜጎች አንድነታቸውን በማጠናከር በኢትዮጵያ እየገጠሙ ያሉ ፈተናዎችን በመመከት ለማሸነፍ ማለፍ እንደሚገባቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ተናገሩ። በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ለሦስት ቀናት የሚካሄደው የፌዴራል የዴሞክራሲ ተቋማት የጋራ ምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ እንደተናገሩት፤ የለውጡ እውን መሆን ሕዝቡን ሲመዘብሩ የነበሩ ቡድኖች ጥቅማቸው መቅረቱን ተከትሎ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ዜጎች ላይ ጥቃት እየፈፀሙ ነው። ከሰሞኑም በነዚህ ቡድኖች ሴራ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በንፁሃን ዜጎች ላይ እጅጉን አሳዛኝ ግድያ የተፈፀመ ሲሆን፤ ተግባሩም እጅጉን የሚያሳዝን ነው፡፡በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ በተለያየ ጊዜ የገጠሟትን ፈተናዎች በልጆቿ የተባበረ ክንድ ማለፏን ያወሱት አፈ-ጉባኤው፤ ከመቼውም ጊዜ በላይ አንድነታችንን በማጠናከር የሚገጥሙንን ፈተናዎች መሻገር ይገባናል ብለዋል። የዴሞክራሲ ተቋማትም ለዜጎች ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር በትኩረት መሥራት ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይሄን ኃላፊነታቸውን ለመወጣትም በተለይም የዴሞክራሲ ተቋማት ነፃና ገለልተኝነታቸውን ጠብቀው ለዜጎች ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን በበኩላቸው፣ የሶማሌ ክልል ከለውጡ በፊት በከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰትና በዜጎች ሰቆቃ የሚታወቅ እንደነበር በማስታወስ፤ የለውጡ አመራር በወሰዳቸው ዘርፈ-ብዙ ማሻሻያዎች የክልሉ ችግር ደረጃ በደረጃ እየተፈታ መምጣቱን ተናግረዋል።በመድረኩ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥራ ኃላፊዎች፣ የምክር ቤቱ የመንግሥት ተጠሪዎችና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች፣ የፌደራል የዴሞክራሲ ተቋማት ኃላፊዎች እንዲሁም የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ሲሆን፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአምስት ዓመት ዕቅድ፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ስላላቸው የሥራ ግንኙነት ተቋማቱን ለማጠናከር በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የማሻሻያ ሥራዎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38148
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ሚያዚያ 27፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር መንግስት በሚያደረገው ጥረት መልካም ጅምሮች ቢኖሩም፤ በተግባር ሂደት እየፈተኑ የሚገኙ ችግሮችን በጋራ በመረባረብ በፍጥነት መሻገር እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን አሳስበዋል፡፡ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት÷የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም አስመልክቶ ከክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር በቪዲዩ ውይይት  ባደረጉበት ወቅት ነው፡፡ህብረተሰቡ ለጥንቃቄ የሚሰጡ መመሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ በማድረግ ረገድ የሚስተዋሉ  ውስንነቶች እና ችግሩን አቅልሎ የማየት አዝማሚያ ፈጣን የባህሪ ለውጥ በሚያመጣ መልኩ መስራት እንደሚጠይቅ በዚሁ ወቅት አንስተዋል።አቶ ደመቀ አያይዘውም  በተግባር ሂደት በየደረጃው የሚስተዋሉ ችግሮችን በመለየት በቀጣይ ወረርሽኙ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል እና የከፋ ዋጋ እንዳያስከፍል በጋራ እንደሚረባረቡ  አሳስበዋል።የክልል ከፍተኛ አመራሮች በበኩላቸው ÷ወረርሽኙን ለመግታት የሚያግዙ አደረጃጀት ፈጥረው አዋጁን ተከትሎ የወጡ መመሪያዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ስለመሆኑ መግለጻቸውን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የፌስ ቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!", "passage_id": "ac7a07846bf5d8edbdde7499d2c8a77a" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ የታየው ለውጥ በጠንካራ ዴሞክራሲያዊ  ስርዓት እስኪተካ ሁሉም የፖለቲካ ሃይላት በተደራጀ እና በሰከነ መንገድ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ አንጋፋዎች ፖለቲከኞች ዶክተር ዲማ ነግዎ እና የኢህአፓ ፓርቲ መሪ ቆንጂት ብርሃኑ ተናገሩ።ፖለቲከኞች ሁለት ዓመት ሊሞላው ጥቂት ወራት የቀሩት አዲስ የለውጥ ምዕራፍ በጠንካራ ተቋማት ግንባታ እና ህዝባዊ ድጋፍ ባላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች መደገፍ አለበት ብለዋል።ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ ይህን እድል በጥንቃቄ መጠቀም ካልቻልን ከአሁን በፊት ያለፉንን ወርቃማ እድል ያከሸፍንበት ታሪክ ሊደገም ይችላል የሚል ስጋታቸውን ተናግርዋል።አንጋፋው ፖለቲከኛ ዶክተር ዲማ ነግዎ አብዛኛውን እድሜያቸው በፖለቲካ እንቅስቃሴ ነው ያሳለፉት፤ እርሳቸው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ከ50 ዓመታት በላይ ያልዘለቀ መሆኑን ተናግርዋል።በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ግን ሁለት ነገሮች የኢትየጵያን ፖለቲካ ወደ ዴሞክራሲ ስርዓት እንዳይሸጋገር አድርገውታል ባይ ናቸው።ቀዳሚው በራሱ የፓርቲዎች ምስርታ በትጥቅ ትግል እና በስውር የጠብመንጃ ፖለቲካ መሆኑ ከዴሞክራሲ ጋር ተላትሟል፤ ሁለተኛው ገዥው ፓርቲ እና የመንግስት ተቋማት የማይለያዩ ሆነው ወጥ አካሄድ መከተሉ ነው ብለዋል።በዚህ መካከል የፖለቲካ ፓርቲዎችም ቁጥር እየተበራከተ የመራጮችን ድምፅ እንዲበታተን እና መሃል ላይ እንዲዋልል አድርጎታል።ዶክተር ዲማ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ግን ሁለት ወርቃማ እድሎች አልፈውናል ባይ ናቸው፤ ቀዳሚ ያደረጉት የ1966ቱን አብዮት እና የክሽፈት ታሪክ ነው።ይህ በጠብመንጃ አንጋቾች የተጠለፈው አብዮት መክሸፍ ብዙ ኢትዮጵያዊያን እያስቆጨ ባለበት ወቅት ፤ሌላ የቁጭት ሌላ የትካዜ ሁነት ደግሞ ተፈጠረ ይላሉ እኒሁ አንጋፋ ፖለቲከኛ፤ ከድህረ ደርግ ወድቀት ማግስት ያለውን አካሄድ በማንሳት።አሁን ደግሞ ተስፋ የተጣለበት የለውጥ እንቅስቃሴ ከተጀመረ ሁለት ዓመት ሊሞላው ጥቂት ወራት ብቻ የቀሩትን ሁነት ያነሱት ዶክተር ዲማ፥ ይህኛው አድል በክሽፈት እንዳይመለስም መጠንቀቅ ያሻል ባይ ናቸው።የእስካሁኖቹ የክሽፈትታሪኮች በገዥ ፓርቲዎች ብቻ አለመሆኑን ለግንዛቤ በማንሳት፤ ሁሉም በጥንቃቄ ሊራመድ ይገባል ባይ ናቸው።በኢትዮጵያ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ እድሜያቸውን ያሳለፉት አሁንም ዳግም አንጋፈውን የፖለቲካ ፓርቲ ኢህአፓን በመሪነት እያገለገሉት ያሉት ወይዘሮ ቆንጅት ብርሃኑ፥ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በሰከነ መንገድ መራመድ አለበት ባይ ናቸው።አንጋፋዋ ፖለቲከኛ ቆንጂት፥ የስሜት ፖለቲካ በርካታ ሀገራትን ዋጋ አስከፍሏል በማለት፤ ድህረ 2011 ሊቢያ እና ሶርያን ለአብነት አንስተዋል።ዶክተር ዲማ ነግዎ የበለፀገች ሀገር ለመመረት ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት  ሊመሰረቱ ይገባል፤ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የሆኑ የደህንነት እና የመከላከያ ተቋማት ሊገነቡ ይገባል ባይ ናቸው።ፖለቲከኛዋ ቆንጂት ብርሃኑም በዚህ ሃሳብ ይስማማሉ።ሁለቱም አንጋፋ ፖለቲከኞች በአንድ ነገር ይስማማሉ፥ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁጥር ከማብዛት ይልቅ፤ ሀገሪቱን እና አለም አቀፍ  ሁኔታውን ያገናዘበ ፖሊስ በመንደፍ መሰባሰብ አለባቸው በሚለው።በስላባት ማናዬ ", "passage_id": "a5392efad698c4876b69961c258e75ab" }, { "passage": "በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አልጠፋም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ትናንት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከመተከል ዞን ነዋሪዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት፤ ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አለመጥፋቱን የገለጹ ሲሆን፤ ምንም እንኳን ጠላቶች በዚህ መልኩ ቢሰሩም አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮች እንዳይደገሙ አድርገን እንፈታዋለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡“ከመተከል ነዋሪዎች\nጋር ባደረግኩት ውይይት ሕዝባችን ለአንድነት፣\nለሰላም፣ ለልማት እና ለብልጽግና ያለው ፍላጎት የትኛውንም\nየመከፋፈል አጀንዳ እንደሚያከሽፍ ተመልክቻለሁ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ በመሆኑ ምክንያትም ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን በጎሳ እና በሃይማኖት የመከፋፈል ፍላጎታቸው አሁንም ድረስ ቢኖርም ይህ ፍላጎታቸው እንዳልተሳካላቸው ገልጸዋል። ይሄንን ጽኑና አስተዋይ ሕዝብ ይዞ ደግሞ ችግሮችን እንዳይደገሙ አድርጎ መፍታት እንደሚቻልም ተናግረዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፣ የሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፤ በመድረኩ ላይ በአካባቢው የተከሰተውን የፀጥታ ችግር መፍታት በሚቻልበት አግባብ ላይ ውይይት የተካሄደበት መሆኑንም ነው ኢዜአ የዘገበው። በተያያዘ፣ ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት እንደዘገበው፤ ውይይቱ መድረኩ በመተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮችን ለማስቆም ዘለቄታዊ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ሲሆን፤ በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለሀገሪቱ አንድነትና ሠላም ብቸኛው አማራጭ ኢትዮጵያውያን ከጥላቻ፣ ከስሜት እና ከመገፋፋት ወጥተው አንድነታቸውን እና አብሮነትን ማጠናከር ነው ብለዋል። በቀጣናው የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር በዘላቂነት ለማስቆም ጥረት የተደረገ ቢሆንም በርካታ ተዋናዮች በመኖራቸው ችግሩን በአፋጣኝ እንዳይቆም አድርጎት መቆየቱንም ገልጸዋል። በመሆኑም አካባቢውን ወደ ሠላም የመመለሱ ሥራ በትኩረት እንደሚሠራ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ባለፈ ግን በዞኑ እየተካሄደ ያለው የህግ ማስከበር ተግባር ገለልተኛ እና ከአድሏዊነት በፀዳ መልኩ እንዲተገበር አሳስበዋል። በስሜት እና በብሶት የጁንታውን የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ ወደ ጫካ የሸሸው ኃይል በሠላማዊ መንገድ እንዲመለሱ ለማድረግ አመራሩና በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።ከዚህ ባለፈ የክልሉን የተፈጥሮ ፀጋ በመጠቀምሥራ አጥ ወጣቶችን በማደራጀት የክልሉ መንግሥት ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እንዲሰራም መልዕክት አስተላልፈዋል። መንግሥት እየወሰደው ካለው እርምጃ ባሻገር በቀጣናው ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶች ጋር በዞኑ የተፈጠረውን የሠላም እጦት ለመፍታት ያላሰለሰ ጥረት እንዲያደርጉም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ ያቀረቡት።የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ኃላፊነት የጎደለው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም እና ባለፋት 27 አመታት የህወሓት ጁንታ የፈፀመው የፖለቲካ አሻጥር በቀጣናው ዘላቂ ሠላም እንዳይረጋገጥ አድርጎ መቆየቱን ተናግረዋል። በመተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚፈጠረውን የጸጥታ ችግር ለማስቆም ጥረት ቢደረግም፤ አባባሽምክንያቶችን ለይቶ መፍትሄ መስጠት ባለመቻሉ የፀጥታ ችግሩ እስካሁን መቀጠሉን አንስተዋል።ዞኑ የተለያዩ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ለዘመናት በአብሮነት የሚኖሩበት አካባቢ እንደመሆኑ መጠን፤ የህዝቦችን አንድነትና አብሮነትን ለማጠናከር መንግሥት በትኩረት ሊሠራ ይገባልም ሲሉ ነው ተሳታፊዎቹ ያስገነዘቡት።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013", "passage_id": "29bb3ebfc54c214f56a34622c0f6eab9" }, { "passage": " አዲስ አበባ፡- ሰዎች በጣም ካልተቸገሩ በስተቀር ከቤታቸው እንዳይወጡ አስገዳጅ ሁኔታ በመፍጠር የኮሮና ወረርሽኝን የመከላከሉ ተግባር ሊተኮርበት ይገባል ሲሉ የተፎካካሪ ፖለቲካ አመራሮች ገለጹ፡፡ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በሽታውን መቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በማተኮር ከመንግሥት ጋር ውይይት እያካሄዱ እንደሚገኙ በመጥቀስ፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አስፈላጊ ከሆነም እንደሚታይ ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሰር መረራ ቀድሞ መከላከል እንጂ ችግሮች ከሰፉ በኋላ ማወጁ ምንም ጥቅም እንደሌለው ተናግረው፤ ችግሩ ሳይሰፋና በሽታው ሳይሰራጭ ሥራዎች መሰራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡ አሜሪካ በመዘናጋት ሀብትና ቴክኖሎጂ ይዛ በርካታ ሰዎች በበሽታው ታምመውባታል ያሉት ፕሮፌሰሩ፤ ኢትዮጵያ ችግሩን ልትሸከመው ስለማትችል ከወዲሁ መሥራት እንደሚያስፈልግና እንደጣሊያንና እስፔን ያሉ አገራት ወረርሽኙ ባደረሰባቸው ተጽእኖ የተነሳ ቀባሪ እስከማጣት የደረሱበት አሳዛኝ ክስተት እንዳይገጥም ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ፕሮፌሰር መረራ ገዥው ፓርቲ ሌሎችን እየከለከለ በየአካባቢው ሰፊ ስብሰባዎች ሲያካሂድ መቆየቱን በማስታወስ እንደሐዋሳ፣ ነቀምት፣ ደምቢዶሎ፣ ሆሳዕና በስፋት እስረኞች አንድ ቦታ ላይ ታጉረው መኖራቸውን ትናንት በስልክ መረጃ እንደደረሳቸው ተናግረው፤ በየማረሚያ ቤቶች ጥቂት ሰውም ቢሞት የማይረሳ ጠባሳ እንዳይጥልና መንግሥት አስሮ አስጨረሰን የሚል ወቀሳ ከማምጣቱ በፊት መፈታት የሚገባቸውን ሰዎች ሕጉን መሠረት በማድረግ እንዲፈቱ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ ሕዝቡ በመከላከል ሥራው መንግሥትን ለመደገፍ የሚያስችል ሥራ እንዲተገብር፣ ሰው በአንድ ልብ በሽታውን መቋቋም የሚችልበትን ኃይል እንዲያሰባስብ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንደሚገባም ተናግረዋል:: አገሪቱንና ሕዝቦችን በተቻለ መጠን በመደገፍ በሽታውን መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ማተኮር እንደሚገባም ፕሮፌሰሩ ጠቁመዋል፡፡ እንደርሳቸው ማብራሪያ፤ በሃይማኖት ተቋማት አካባቢ ያለው ነገር መስተካከል አለበት፡፡ ሰዎች በተቀራረበ መንገድ ወደእምነት ስፍራ እንዳይጓዙ ሊደረግ ይገባል፡፡ ሃይማኖትም የሚኖረው ሕይወት ሲቀጥል በመሆኑ የሃይማኖት አባቶች ሁኔታውን ለመቀየር፣ መንግሥትም ሕይወት ለማትረፍ ጠበቅ ያለ ሥራ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የቀድሞው የመኢብን፤ የአሁኑ የአነን (የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ንቅናቄ) ፕሬዚዳንት ልጅ መስፍን ሽፈራው፤ መንግሥት የአገር ሽማግሌዎችንና የሃይማኖት አባቶችን ጭምር በማስተባበር እስካሁን አቅሙ በፈቀደ መንገድ ቢሰራም የሕዝቡ አለመታዘዝ ክፍተት እንዳለው መታዘባቸውን ይናገራሉ፡፡ ፕሬዚዳንቱ በእምነት ተቋማት፣ በትራንስፖርት አጠቃቀም እና በገበያ አካባቢዎች ላይ የሚታዩ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት ጥረት በማድረግ ኅብረተሰቡ የራሱን የቤተሰቡንና የወገኑን ሕይወት ሊታደግ ይገባዋል ሲሉ መክረዋል፡፡ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እያደረጉት ያለው እንቅስቃሴ አበረታች ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ የአገር ውስጥን ከማስተባበር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሁኔታውን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል እንቅስቃሴ መኖሩን እንዳስተዋሉና በተያዘው የመከላከል አጀንዳ የተለየ ሃሳብና ቋንቋ እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በድህነት ውስጥ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ሕይወት ለመታደግ ቤት ለሌላቸው ቀድሞ መጠለያ ማዘጋጀት እንደሚገባና የዕለት ቀለባቸውን ለማሟላት አስፈላጊ መሆኑን፤ ችግሩ ቢሰፋ እንኳ ሕክምናውን ለመቆጣጠር ሥራዎችን ቀድሞ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን መጋቢት 30/2012\nዘላለም ግዛው", "passage_id": "baa36a6f74345b2d67a9393c9dfecf42" }, { "passage": " ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ዙሪያ እየተወሰዱ ባሉ እርምጃዎች ዙሪያ ከትናንት በስቲያ ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ጋር በጽህፈት ቤታቸው መወያየታቸው ይታወቃል ። ኮቪድ-19 በኢትዮጵያ ላይ በሚያሳድረው ተጽዕኖና መንግሥት የሚወስዳቸውን ተጨማሪ እርምጃዎች አስመልክቶ የተደረገው ውይይት ገንቢ እንደነበር ማስታወቃቸውም ይታወሳል ።በውይይቱ ላይ ከተሳተፉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች መካከል ዶክተር አረጋዊ በርሄ ይገኙበታል። ዶክተር አረጋዊ የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ አመራር ናቸው። በወቅቱም ኮረና ቫይረስ በአገር ላይ የመጣ ችግር መሆኑን በመጥቀስ፣ መደረግ ስለሚገባው ርምጃ በስፋት ውይይት መካሄዱን ይናገራሉ። በመንግስት በኩል መደረግ ስለሚገባቸው ጉዳዩች የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ማብራሪያ መስጠታቻውን እና ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድም (ዶክተር) ማስገንዘቢያ ማቅረባቸውን አስታውቀዋል። ‹‹እንደ ፖለቲካ ፓርቲ አመራርና አባል ማድረግ ስለሚገባን ተወያይተናል›› የሚሉት ዶክተር አረጋዊ፤ ሁሉም የፖለቲካ ፖርቲ አመራሮች ሰፊ ውይይት በማድረግ ለጉዳዩ ትኩረት እንደሰጡት መገንዘባቸውን ነው የጠቆሙት። ‹‹ባለሙያዎች የሚሰጡትን መፍትሄ ግምት ውስጥ በማስገባት ወረርሽኙን መከላከል የሁሉም ሃላፊነት ሊሆን ይገባል፤ ዋናው መፍትሄም ይሄው ነው›› ያሉት ዶክተር አረጋዊ፣ ህዝቡም ግንዛቤውን እንዲያሰፋ ማድረግ ይጠበቃልም ብለዋል። በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ክፍተቶች እንዳሉ ማስተዋላቸውንም አስታውቀዋል።የወረርሽኙ ክብደት የከፋ መሆኑን ግንዛቤ እንዲወሰድ መሰራት እንዳለበት አመልክተው፣በተለይም በአንዳንድ የእምነት ተቋማት እና የገበያ ስፍራዎች ላይ በሰዎች መሰባሰብ የሚታይ ግዴለሽነት እንዲስተካከል የድርሻቸውን ለመወጣት መተማመን ላይ መደረሱንም ነው የገለጹት። እንደ እርሳቸው ማብራሪያ፤ የጤና ባለሙያዎች የሚሰጡትን ምክረ ሃሳብ እና ሊተገበሩ የሚገባቸውን ጥንቃቄዎች መፈጸም ይገባል። በየእምነት ተቋማት፣ በገበያ ስፍራዎች፣ በትራንስፖርት መጠበቂያዎች፣ በየሱቆች እና በተለያዩ ስፍራዎች መሰባሰብን ማስወገድ እና መቆጠብ ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በበኩላቸው እንደገለፁት፤ የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ታክሞ ማዳን የማይቻል አስቸጋሪ በሽታነው። የትኛውም የህብረተሰብ ክፍል ከዚህ ወረርሽኝ ለመጠበቅ በጤና ባለሙያዎች የሚሰጠውን የመከላል ሂደት መተግበር አለበት። ‹‹የአኗኗር ደረጃችንን አነስተኛ በመሆኑ እንደ በለፀጉት አገራት በራችንን ከርችመን ለመቀጠል እንቸገራለን። ምክንያቱም የየዕለት ጉርስ ማግኘት ግድ የሚለው የሕብረተሰብ ክፍል በመኖሩ እንቅስቃሴዎች አይጠፉም።››ያሉት ፕሮፌሰር በየነ፣ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ራስን መጠበቅ በወረርሽኙ ላለመያዝ ዋናው ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል። ‹‹ወቅቱ የበልግ ነው፤ አርሶ አደሩ ማረስ ይጠበቅበታል።›› ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ በዚህ ወሳኝ ወቅት አንዳንድ አርሶ አደሮች ቤት መቀመጣቸውን ከአንዳንድ አካባቢ ከሰሙት መረጃ መረዳታቸውን አስታውቀዋል።‹‹ይህ የሚመከር አይደለም፤ አርሶ አደሩ እንደቀደመው ጊዜ የደቦ አይነት አካሄድን በማቆም ስራውን በግል ሊያከናውን ይገባል›› ብለዋል። እርሳቸው በፓርቲያቸው አማካይነት ደጋፊዎቻቸውን መሰረት አድርገው ህዝቡ ከኮረና ቫይረስ ራሱን እንዴት መከላከል እንዳለበት ግንዛቤ በማስጨበጥ ላይ እንዳሉ አመልክተው፣ ወቅቱ ስብሰባን የሚከለክል እንደመሆኑም ደጋፊዎቻቸው ቤት ለቤት ጭምር በመንቀሳቀስ ግንዛቤ የማስረፁን ስራ እንደተያያዙትም አስረድተዋል። ፕሮፌሰር በየነ እንደተናገሩት፤ ወረርሽኙን አስመልክተው የሚወጡ መልዕክቶችን በታቻለ መጠን የተለያዩ ቋንቋዎችን በመጠቀም ማስተላለፍ ይገባል።ፓርቲያቸውም ከዚህ አኳያ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ሲሆን፣ ድምፅ ማጉያን በመጠቀምም መልዕክቱን እያደረሰ ይገኛል። ፕሮፌሰሩ በኬንያ በኩል በህገ ወጥ መንገድ ወጥተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ አገራቸው በዚያው በኬንያ በኩል እንዲመለሱ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ እነዚህ ልጆች ወደዱራሜ ዘልቀዋል ተብሏልና መላ ቢበጅ መልካም ነው ሲሉ አስገንዝበዋል። መንግስት በዚህ ላይ እንዲሰራ ጠይቀው፣ አገሪቱ ዜጋዋን የትም አትጥልምና ይህን ተከትሎ ለይቶ ማቆያ ቢያንስ በየዞኑ ማዘጋጀት እንደሚገባ ጠቁመዋል። የየዞኑን ባለሀብትም በማነሳሳት ይህን ማዘጋጀት እምብዛም እንደማይከብድ አስታውቀዋል። አዲስ ዘመን መጋቢት 29/2012 በጋዜጣው ሪፖርተሮች", "passage_id": "d0a18b473a89b0f88c09d45ae480295b" } ]
961620557992b77d8348dc2e420a5135
16afa0688866b1803cf512890d1cbb51
በወሰን አካባቢ የተከሰተው ግጭት የሁለቱ አገራትን ሕዝቦች እና መንግሥታት አለመሆኑ ተገለጸ
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ እና የሱዳን ወሰን አካባቢ የተከሰተው ግጭት የሁለቱ አገራትን ሕዝቦች እና መንግስታት የማይወክል፤ ይልቁንም በሁለቱ አገራት ሕዝቦች መካከል ጥርጣሬ እና ግጭት እንዲፈጠር ድብቅ አጀንዳ ይዘው የሚንቀሳቀሱ አካላት ሴራ መሆኑንም ነው የተገለጸው።እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ክስተቱን አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት በአረብኛ ባወጣው መግለጫ የተፈጠረው ችግር የኢትዮጵያም ሆነ የሱዳን መንግስት ፍላጎት አይደለም። እንዲያውም በሁለቱ አገራት ሕዝቦች መካከል ጥርጣሬ እና ግጭት እንዲፈጠር ድብቅ አጀንዳ ይዘው የሚንቀሳቀሱ አካላት ሴራ መሆኑን መንግስት ይገነዘባል። ይሁን እንጂ ሁለቱ አገራት ችግሩን በጋራ በሠላማዊ ውይይት ለመፍታት ጥረት እንደሚያደርጉ የኢትዮጵያ መንግስት አስታውቋል::ግጭቱ መፈጠሩ አሳዛኝ ቢሆንም በተለይም የኢትዮጵያ መንግስት በሰሜናዊ የአገሪቱ ክፍል ሕግ የማስከበር ስራውን አጠናቆ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት እያከናወነ ባለበት ወቅት እና በተመሳሳይ መልኩ ሱዳን ደግሞ በሕዝባዊ ተቃውሞ የተነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ ደፋ ቀና በምትልበት ጊዜ መፈጠሩ የበለጠ አሳዛኝ እንደሚያደርገው የኢትዮጵያ መንግስት ባወጣው መግለጫ አመልክቷል:: በሱዳንና ኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ የተከሰተው የፀጥታ ችግርም የኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስትን የሚመጥንና የሚወክል አለመሆኑንም መግለጫው አስታውቋል:: ለዘመናት የዘለቀው የሁለቱ አገራት እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት በሴረኞች እንደማይሰናከል የገለፀው መግለጫው፣ የሁለቱ አገራት ሕዝቦች ነጻነታቸውን ከማረጋገጥ ባሻገርም፣ ከራሳቸው አልፈው ለአካባቢውም ጭምር ስልጣኔና ቅርስ አበርክቷቸው በጋራ የሚያስተሳስራቸው መሆኑም ተመልክቷል::በፈተናም ጊዜ የሁለቱ አገራት ሕዝቦች ሲተጋገዙ እንደነበር በመግለጽም፣ በአሁኑ ጊዜም ቢሆን በዓለም አቀፍ መድረኮች ጭምር ኢትዮጵያ እና ሱዳን የጋራ ጥቅሞቻቸውን በአብሮነት በማስከበር ላይ መሆናቸውንም መግለጫው አስታውሷል፣ይህም ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን አገራቱ ለዘመናት ባዳበሩት አብሮነት ጭምር የተገኘ እሴት መሆኑን ተመልክቷል::በሱዳን በቅርቡ የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ አብዮት ሕዝቡ በፍላጎት ያደረገው በመሆኑ እንዲሳካም ኢትዮጵያ ከሱዳን ሕዝብ እና መንግስት ጎን በመቆም ሠላም እና መረጋጋት እንዲመጣ ስታግዝ ቆይታለችም ብሏል:: ይህም በሁለቱ አገራት እና ሕዝቦች መካከል ያለውን ወንድማዊ ግንኙነት የሚያሳይ መሆኑንም መግለጫው አመልክቷል::ይሁን እንጂ በቅርቡ አንዳንድ አካላት በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ግጭት ለመፍጠር የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ የኢትዮጵያ መንግስት በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን አስታውቋል:: ድርጊቱንም ሁለቱ አገራትን የማይወክል እና የተፈጠረውን ችግር በሠላማዊ ውይይት እንደሚፈቱት የኢትዮጵያ መንግስት አቋሙን ገልጿል::አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38074
[ { "passage": "ይሁን እንጂ በማንኛውም ሰዓት ሊያገረሽ እንደሚችል ነዋሪዎቹ እየተናገሩ ናቸው። እስከአሁን በነበረው ግጭት የአምስት ሰው ሕይወት መጥፋቱና 15 ሰው መቁሰሉ ተሰምቷል።በሁለቱም ወገኖች የሚታየው እልህ እና ሦስቱን አወዛጋቢ ቀበሌዎች የሚታየው አንዱ ለሌላኛው ለመልቀቅ ፈቃደኛ ያለመሆን አዝማሚያ ለቀጣይ ግጭቶች መንስዔ ሊሆን እንደሚችል የሚናገሩ ታዛቢዎች ሥጋታቸውን እየገለፁ ነው። ", "passage_id": "18659138672e7ea20fb0541615c5b9b8" }, { "passage": "ምንም እንኳን በሁለቱ ህዝቦች መካከል ፀብ ባይኖርም በመሀከላቸው ግጭት እንዲፈጠር የሚያደርጉ ኃይሎችን በጋራ መንጥረው በማውጣት ለህግ እንዲቀርቡ ለማድረግ ታስቦ ነው ዕርቀ ሰላሙ የተካሄደው ይላሉ የሁለቱ ወረዳ አስተዳዳሪዎች። ", "passage_id": "bf937d187b579297df1ed123844921a0" }, { "passage": "የበርካታ ዜጎች ሕይወት አልፏልበኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ከሰሞኑ የተቀሰቀሱት ግጭቶች፣ ሥውር የፖለቲካ ተልዕኮ የያዘና ምሥራቅ አፍሪካን በግጭት የመረበሽ አዝማሚያ የታየበት መሆኑ ተገለጸ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መከላከያና ፌዴራል ፖሊስ በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተሠማርተው፣ የግጭቱን ተሳታፊዎችን በአነስተኛ ኪሳራ በቁጥጥር ሥር በማዋል ለሕግ እንዲያቀርቡ ሰኞ ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ.ም. ትዕዛዝ መስጠታቸው ይታወሳል፡፡የተቀሰቀሰውን ግጭት በተመለከተ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የካቢኔ አባልና የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፣ በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት በመቀስቀሱ ቀጣናዊ ግጭት የመቀስቀስና አካባቢውን የመረበሽ አዝማሚያ መኖሩን አስረድተዋል፡፡‹‹አንዳንዴ በሲቪል አንዳንዴ ደግሞ የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ ወታደራዊ የደንብ ልብስ በመልበስ፣ ከባድ መሣሪያ ታጥቀውና ተሽከርካሪዎችን ተጠቅመው በአዋሳኝ የኦሮሚያ አካባቢዎች በመዝለቅ ነዋሪዎችን ተኩሶ የመግደልና ቤቶችን የማቃጠል ጥቃቶች ሰሞኑን ተፈጽመዋል፤›› ብለዋል፡፡በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች አርብቶ አደሮች በመሆናቸው፣ ከብቶቻቸውን ለመጠበቅ ከረዥም ጊዜ አንስቶ መሣሪያ የመታጠቅ ልምድ እንዳላቸው ያስታወሱት ኃላፊው፣ ጥቃት ሲደርስባቸው አፀፋዊ ዕርምጃ መውሰዳቸውንም ተናግረዋል፡፡ይሁን እንጂ ከሶማሌ ወገን አንድ ሰው ሲሞት በጎረቤት አገሮች የሚገኙ ተመሳሳይ ጎሳ አባላት እንዲሳተፉ፣ ‹‹ኦሮሞ ገደለን›› የሚል መረጃ በፍጥነት እንደሚሰራጭና በግጭት የመነገድ አዝማሚያ መኖሩን  አስረድተዋል፡፡የዚህ እንቅስቃሴ ዓላማ ፖለቲካዊ ግብ የያዘ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል እንደሚገነዘብ የተናገሩት ነገሪ (ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ክልልን በማተራመስ ማዕከላዊ መንግሥትን ማዳከም እንደሆነ አስረድተዋል፡፡የግጭቱ ፈጻሚዎች መቀመጫቸውን በሶማሌ ክልል በማድረግ ከመሀል አገር እስከ የተለያዩ ጎረቤት አገሮች የተዘረጋ ሰንሰለት እንዳላቸው፣ ከፌዴራል መንግሥት እስከ ክልል የፀጥታ መዋቅሮች የዚህ ኔትወርክ አባሎች እንደሚገኙም መረጃ መኖሩን ጠቁመዋል፡፡ከዚህ ቀደም በምሥራቁ የአገሪቱ ክፍል በከፍተኛ የዶላር ማስተላለፍና የኮንትሮባንድ ንግድ ላይ የተሰማራው ከመሀል አገር አንስቶ እስከ ጎረቤት አገሮች የተደራጀውና የጉምሩክን መዋቅር የሚጠቀመውን ቡድን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርና አስተዳደራቸው መበጣጠስ በመጀመራቸው፣ ህልውናቸውን ለማስቀጠል የተቀሩት የቡድኑ አባላት ከጀርባ ሆነው ስፖንሰር የሚያደርጉት ግጭት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ሥልጣን በያዙ በማግሥቱ ወደ ሶማሌ ክልል በማቅናት በሁለቱ ክልሎች መካከል ባለፈው ዓመት የተከሰተው አሰቃቂ ግጭትና መፈናቀል እንዳይደገም፣ ለዚህም የሁለቱ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች በጋራ እንዲሠሩ በማሳሰብና እጅ ለእጅ በማያያዝ ቃል አስገብተው መመለሳቸው ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ ወደ ሰላም ለመምጣት ያስፈልጋሉ የተባሉ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙቶች እስካሁን አልተካሄዱም፡፡‹‹መታወቅ ያለበት ጉዳይ በሁለቱ ክልሎች ሕዝቦች መካከል የተፈጠረ ግጭት የለም፡፡ የወሰን ጉዳይ በተካሄደው ሕዝበ ውሳኔ ምላሽ አግኝቷል፡፡ በተደጋጋሚ እየተፈጠረ ያለው ግጭት ፈጽሞ ሕዝባችን አይወክልም፤›› ያሉት ነገሪ (ዶ/ር)፣ ከሶማሌ ክልል አመራሮች ጋር በመነጋገር የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱን ለመጀመርም ትልቅ ኮንፈረንስ በአዳማ እንዲካሄድ ስምምነት ተደርሶ ቀን ተቆርጦ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ስብሰባው ሊካሄድ ሳምንት ሲቀረው የረመዳን ፆም የሚገባ በመሆኑ ከፆሙ በኋላ እንዲሆን ጥያቄ በመቅረቡ መተላለፉን፣ ከፆሙ በኋላ ግን ግጭት በመቀስቀሱ ማካሄድ አለመቻሉን ያስረዳሉ፡፡‹‹የሶማሌ ክልል አመራሮች ለሰላም ዝግጁ ስለመሆናቸው ከሚነግሩን እንረዳለን፡፡ አሁንም ቢሆን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱን ለመጀመርና ሁለቱ ክልሎች በሚመሩት ፓርቲዎች መካከል ውይይት እንዲካሄድ፣ ርዕሳነ መስተዳድሮቹ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፤›› ሲሉ አክለዋል፡፡በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት በኩል የተቀሰቀሰውን ግጭት አስመልክቶ መረጃ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ አልተሳካም፡፡ግጭቶቹ እየተከሰቱ የሚገኙት በምዕራብና በምሥራቅ ሐረርጌ አካባቢዎች በጭናክሰን፣ በባቢሌ፣ በሚኤሶ እንዲሁም በቦረና፣ በጉጂና በሞያሌ አካባቢዎች እንደሆነ ነገሪ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡በምዕራብ ኦሮሚያ በኩል የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አካል የሆነ አንድ የታጠቀ ቡድን የፖሊስ ተቋማትና ፖሊሶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ሲፈጽም የነበረ ቢሆንም፣ ባለፈው ሳምንት መረጋጋት ታይቶ እንደነበር ነገሪ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ ተመሳሳይ ጥቃት ሰኞ ሐምሌ 9 ቀን 2010 ዓ.ም. በቄለም ወለጋ በመንቀሳቀስ ላይ በነበረ አንድ የክልሉ ፖሊስ ተሽከርካሪ ላይ መሰንዘሩን አስታውቀዋል፡፡መንግሥት ማንኛውም የፖለቲካ ኃይል ወደ አገር ገብቶ በሰላማዊ መንገድ ይታገል ባለበትና ከኦነግ ጋርም ውይይት ለመጀመር ዝግጅት ላይ ሳለ፣ ይህ ድርጊት መፈጸሙ ተገቢ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡የአገር መከላከያ ሚኒስትር አቶ ሞቱማ መቃሳ ማክሰኞ ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት የፀጥታ ችግር ባጋጠማቸው አካባቢዎች የመከላከያ ሠራዊት የማረጋጋት ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡ የሁለቱም ክልሎች አመራሮች የፌዴራል መንግሥት የፀጥታ ኃይል እንዲገባ በወሰኑት መሠረት፣ የመከላከያ ሠራዊትና ፌዴራል ፖሊስ በተመረጡ ሥፍራዎች እየገቡ መሆናቸውንም ሚኒስትሩ አክለዋል፡፡ሰሞኑን እያጋጠሙ ያሉ ግጭቶች ከወትሮው ለየት ያሉና ስፋት ያላቸው አካባቢዎችን መሸፈናቸውን ገልጸው፣ የበርካታ ዜጎች ሕይወት ማለፉን ጠቁመዋል፡፡ ከግጭቱ በስተጀርባ ያሉ አካላት በአገሪቱ እየታየ ያለውን ሰላምና መረጋጋት የማይፈልጉ ኃይሎች መሆናቸውን፣ በቅርቡም ማንነታቸው እንደሚገለጽ አስታውቀዋል፡፡ በመከላከያ ሠራዊቱ አማካይነትም ግጭቶች በአጭር ጊዜ እንደሚቆሙና ሰላምና መረጋጋት እንደሚፈጠር ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "102a8aec95e5d4977c14844570861462" }, { "passage": "በኢትዮጵያና በኬንያ ድንበር አካባቢ በነዋሪዎች መካከል አሁንም ግጭቶች መኖራቸውን  የሪፖርተር ምንጮች አመለከቱ፡፡በሁለቱ አገሮች ድንበር አካባቢ በነዋሪዎች መካከል ባለፈው ሳምንት በተቀሰቀሰ ግጭት፣ የሰው ሕይወትና ንብረት መውደሙንም ለማወቅ ተችሏል፡፡በቅርብ ርቀት ባሉ የድንበር አካባቢዎች ግጭት የተከሰተ ቢሆንም፣ መንስዔው ምን እንደሆነ ለማወቅ ሪፖርተር ያደረገው ጥረት ግን አልተሳካም፡፡ከሁለት ዓመት በፊት በድንበር አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ሦስት የኬንያ ፖሊሶችን ከገደሉ በኋላ በሁለቱ አገሮች መካከል አልፎ አልፎ ግጭቶች ሲከሰቱ እንደነበር የዓይን እማኞች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ የሦስቱ የኬንያ ፖሊሶች ግድያ የሁለቱን አገሮች መንግሥታት ቅራኔ ውስጥ ከቶ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ሁለቱ አገሮች በሚዋሰኑባቸው የድንበር አካባቢዎች አልሸባብ እንደሚንቀሳቀስ፣ ለሁለቱ አገሮች አልፎ አልፎ ግጭት መከሰትም ድርሻ እንዳለው መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡በተደጋጋሚ ጊዜ በሁለቱ አገሮች መካከል እየተፈጠረ ያለውን ግጭት ለመፍታት ሲባልም፣ የፌዴራልና አርብቶ አደር ልማት ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ካሳ ተክለ ብርሃን ሐሙስ ሰኔ 15 ቀን 2009 ዓ.ም. ወደ ኬንያ አቅንተው ነበር፡፡ በሁለቱ አገሮች መካከል እየተከሰተ ያለውን ግጭት ለመፍታት ከኬንያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ውይይት ተቀምጠዋል፡፡  ሁለቱ አገሮች በሚዋሰኑበት አካባቢ በሚኖሩ አርብቶ አደሮች መካከል የሚፈጠረውን ግጭት ለመፍታት ወደ ኬንያ ያቀኑት አቶ ካሳ፣ በሚደረሰው ስምምነት መሠረት በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ኅብረት ከማጠናከሩ በተጨማሪ በቀጣናው እየተፈጠረ ያለውን ግጭት ሊፈታ እንደሚችል ተናግረዋል፡፡የፌዴራልና አርብቶ አደር ልማት ጉዳዮች ሚኒስቴር የኮሙዩኒኬሸን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አበበ ወርቁ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ቦረናና ዳዋ ዞኖችን ከሚያዋስኗቸው የኬንያ አካባቢዎች ነዋሪዎች ጋር አልፎ አልፎ እየተፈጠረ ያለውን ግጭት ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመፍታት ታስቦ ስምምነት መደረጉን ገልጸዋል፡፡እንደ አቶ አበበ ገለጻ በሁለቱ አገሮች መካከል በሚኖሩ ዜጎች መካከል ያለውን ችግር ለመፍታት የጋራ ፕሮጀክቶች ሰነድ ተዘጋጅቶ፣ ከሁለቱም አገሮች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ሲወያዩበት ቆይተዋል፡፡ የዚህ ሰነድ ዋነኛ ዓላማም በአካባቢው ላይ ሰላምን በማስፈን ዘላቂ ልማት በማምጣት ኅብረተሰቡን ከድህነት ማላቀቅ፣ እንዲሁም ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በተሟላ መንገድ በጋራ ለመገንባት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡በሁለቱ አገሮች መካከል ሲፈጠር የነበረውን ግጭት ከማስወገድ በተጨማሪ፣ በሰባት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ መፍትሔ በመስጠት ውጤት ለማምጣት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ሁለቱ አገሮች ስምምነት ላይ የደረሱባቸው ጉዳዮች ሰባት ሲሆኑ፣ እነሱም በሀብት ሽሚያ ምክንያት የሚፈጠረውን ግጭት መከላከል፣ በአካባቢው የገበያ ንግድ ትስስር እንዲጠናከር ማድረግ፣ የተፈጥሮ ሀብት አያያዝና አጠቃቀም፣ የእንስሳት ሀብት ልማትና የኅብረተሰቡ ተጠቃሚነት፣ የአደጋ ተጋላጭነትን መከላከልና ማስወገድ፣ የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግርና የጋራ ተቋማትን የመገንባት ስምምነቶች እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡ ይህ የጋራ ስምምነት ሁለቱ አገሮች በጋራ ፋይናንስ የሚያደርጉበትና ዕርዳታ የሚገኝበት ፕሮጀክት እንደሆነ አቶ አበበ አክለዋል፡፡ወደ ኬንያ አብረው ካቀኑት ከፍተኛ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት መካከል የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ለማ መገርሳና የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ተወካይ ይገኙበታል፡፡ ኢትዮጵያን ወክለው ስምምነቱን የፈረሙት አቶ ለማ፣ ‹‹ይህ የስምምነት ፕሮጀክት በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን የአርብቶ አደር ሕይወት የሚቀይር በመሆኑ ፋይዳው የጎላ ነው፤›› ብለዋል፡፡ አቶ ለማ መገርሳ የክልሉ ፕሬዚዳንት ሆነው ወደ ሥልጣን ከመጡ ወዲህ ከወሰዷቸው ዕርምጃዎች መካከል የኦሮሚያን ክልል ከሚያዋስኑ ክልሎች ጋር ያለውን አስተዳደራዊ ወሰን ማካለል ተጠቃሽ ነው፡፡ ይህ የአቶ ለማ ወደ ኬንያ ማቅናትም የኦሮሚያ ክልል በድንበር አካባቢው ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት ለሚያደርገው እንቅስቃሴ ሌላው ማሳያ እንደሆነ እየተነገረ ነው፡፡ኢትዮጵያና ኬንያ አልፎ አልፎ በድንበር አካባቢ ከሚፈጠረው ግጭት ባሻገር፣ የኦሞ ወንዝ ላይ የኃይል ማመንጫ በመገንባቱ ኬንያ ቅር መሰኘቷን ሰሞኑን እየወጡ ያሉ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ከቱርካና ሐይቅ ዓሳ በማስገር የሚኖሩ ኬንያውያን በሐይቁ መቀነስ ምክንያት ችግር ውስጥ መግባታቸው እየተነገረ ነው፡፡ ለቱርካና ሐይቅ ዋነኛ ገባር የሆነውን የኦሞ ወንዝ ኢትዮጵያ ለኃይል ማመንጫ መጠቀሟ ሐይቁ እየቀነሰ በመምጣቱ የኬንያ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሰሞኑን ጥያቄ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ወደ ኬንያ ያቀኑት አቶ ካሳ በሁለቱ አገሮች መካከል ከተከሰተው ግጭት ባሻገር፣ በሁለቱ አገሮች መካከል ባሉት ተሻጋሪ ወንዞች ጉዳይ ከኬንያ መንግሥት ጋር እንደሚነጋገሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ", "passage_id": "efe6f14d2a5fa7a94c79c6ecf895e524" }, { "passage": "የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እንዳሉት የግጭቱ ምክንያትድንበር ተሻግረው የገቡ የሱዳን ወታደሮች ናቸው::የትግራዩን ሕግ የማስከበር ዘመቻ ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዩች መጠመዳችንን እንደ ጥሩ አጋጣሚመጠቀም የፈለጉ ያሏቸውን የሱዳን የበታች ባለስልጣናትም ተጠያቂ አድርገዋል::የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ቀዱም ሲል ባወጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ወታደሮችናሚሊሽያዎች ወደ ግዛትችን በመግባት ከቅኝት ሲመለሱ በነበሩ የፀጥታ ሃይሎቻችን ላይ ጥቃት ፈፅመዋል ብለዋል::ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ “ጦርነት በተቀሰቀሰበት የትግራይ ክልል አቅራቢያ በሚገኘው አጎራባቹ የኢትዮጵያድንበር አካባቢ ባለው የሱዳን የእርሻ መሬት ላይ ሱዳን ሠራዊቷን ማሠማራቷን ቀጥላለች” ሲሉ አንዳንድየሱዳን ባለሥልጣናት ባለፈው ሣምንት ተናግረው ነበር።መንግሥት በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ከአካባቢ ሚሊሻ ጋር የተፈጠረውን ክስተት በቅርበት እየተከታተለውመሆኑን ጠቅላይ ሚስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ፡፡\"ሁለቱ ሀገራት እንዲህ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ሁሌም የውይይትን አማራጭ የሚከተሉ በመሆናቸውክስተቱ የሁለቱን ሀገራት ጥብቅ ትስስር አያላላውም\" ብለዋል ጠቅላይ ሚስትሩ በትዊተር ገፃቸው ላይባሰፈሩት አስተያየት፡፡\"ክስተቱን እንደ መልካም አጋጣሚ ወስደው በማራገብ ልዩነትን ለማስፋት የሚጥሩ አካላት የሁለቱንሀገራት ታሪካዊ ትስስር ያልተረዱ ናቸው\" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)\n ", "passage_id": "2805cfe603b21cbbb1a6b666422ff896" } ]
dae585d5c89d5daab9339fa0e56ccab5
c1a3934ef128e2c24bafaf397641a09b
ኬንያዊው አትሌት የአስር ዓመቱ ምርጥ ተሰኝቷል
ባለፉት አስር ዓመታት በአትሌቲክስ ስፖርት ውስጥ በርካታ ክስተቶች ተስተናግደው አልፈዋል። ለቁጥር የሚታክቱ ክብረወሰኖች ከመሻሻላቸውም ባለፈ በሰው ልጅ ሊደፈሩ ይችላሉ በሚል የማይጠበቁና የማይገመቱ ታሪካዊ ክንውኖችም ታይተዋል። ከእነዚህ መካከል በተለይ በስፖርቱ አጭር ርቀት ውድድር (100ሜትር) እና በረጅሙ ርቀት (ማራቶን) የተመዘገቡት ስኬቶች የሰውን ልጅ አቅም በትክክልም ማሳየት የሚያስችሉ ሆነዋል። ታዲያ በአስሩ ዓመታት ከታዩና ክብረወሰንም ካስመዘገቡ አትሌቶች መካከል የተሻለው ማን ነው? በዚህ ጥያቄ ላይ ተንተርሶ ምርጫውን ያካሄደው ደግሞ እአአ በ1940 መሰረቱን በአሜሪካ በማድረግ የተቋቋመውና ትኩረቱን በመምና ሜዳ ተግባራት ስፖርቶች ላይ ያደረገው መጽሄት ነው። መጽሄቱ እአአ ከ2010-2019 ድረስ ባሉት ዓመታት ከጎዳና ላይ ውድድሮች ባሻገር ባሉት ውድድሮች አስር አትሌቶችን በእጩነት በማቅረብ ምርጫውን በአዲሱ የፈረንጆች ዓመት መጀመሪያ ነበር የጀመረው። በተሰጠው ድምጽ መሰረትም ኬንያዊው የ800 ሜትር አትሌት ዴቪድ ሩዲሽያ ተመራጭ ሊሆን ችሏል። በእጩነት ከቀረቡት አትሌቶች መካከል አንዱ በአጭር ርቀት የአትሌቲክስ ተጽእኖ ማሳደር የቻለው ጃማይካዊ አትሌት ዩሲያን ቦልት ነው። አሁን ራሱን ከተወዳዳሪነት ያገለለው ቁመተ መለሎ አትሌት በ100 ሜትር የሸፈነበት 9ሰከንድ ከ63 ማይክሮ ሰከንድ የምንጊዜም የርቀቱ ምርጥ አትሌት ያደርገዋል። በውድድር ተሳትፎው ከደረጃ ወርዶ የማያውቀው አትሌት አራት የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያዎችን ከማጥለቅ ባሻገር የዓለም ቻምፒዮን በመሆንም ክብረወሰኑን አርቆ የሰቀለ አትሌት መሆኑ ምርጫውን በአሸናፊነት ያጠናቅቃል በሚል ይጠበቅ ነበር። በረጅም ርቀት የመም ላይ ውድድሮች በኢትዮጵያዊያኑ ጀግና አትሌቶች እግር የተተካው እንግሊዛዊ አትሌት ሞሃመድ ፋራም በእጩነት ከቀረቡት መካከል ነበር። የዓለም ቻምፒዮናው በኦሊምፒክ አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ያሳካ ሲሆን፤ በ5ሺ እና 10ሺ ርቀቶች ሃገሩን በተደጋጋሚ ለማስጠራት ችሏል። አትሌቱ ምንም እንኳን ከመም ወደ ጎዳና ላይ ውድድሮች ባደረገው ሽግግር እንደሚጠበቀው ውጤታማ ባይሆንም ያለፉት አስር ዓመታት ግን ለእርሱ አስደሳች ነበሩ። ከመም ይልቅ በማራቶን ስሙ የገነነውና የዚህ ወቅት የርቀቱ ቁጥር አንድ አትሌት የሆነው ኬንያዊ ኢሉድ ኪፕቾጌም ቀዳሚ ተመራጭ ይሆናል በሚል ከሚጠበቁት እጩዎች መካከል ነበር። የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ እንዲሁም ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች የመግባት ሙከራውን ያሳካው አትሌት በሮጠበት ጫማ ምክንያት ውዝግቦችን ያስተናግድ እንጂ የጎዳና ላይ ሩጫዎች ንጉስነቱን ማንም ሊቀማው እንደማይችል ነው አዘጋ ጆቹ ያረጋገጡት። አሜሪካዊያኑ ክርስ ቲያን ቴይለርና አሽተን ኢትን፣ ደቡብ አፍሪካዊው ዋይዴ ቫን ኔኬርክ፣ ፈረንሳ ዊው ሬናውድ ላቪሌኔ፣ የኳታሩ ሙታዝ ባርሺም እንዲሁም ጀርመናዊው ሮበርት ሃርቲንግም ከአስሩ እጩዎች መካከል ይገኙበታል። ከእጩዎቹ መካከል በተለይ ‹‹የዓለም ፈጣኑ ሰው›› በሚል የሚታወቀው ጃማይካዊ አትሌት አብላጫውን ድምጽ ያገኛል የሚል ግምት ያግኝ እንጂ አሸናፊ የሆነው ግን ዴቪድ ሩዲሽያ ነው። የለንደንና ሪዮ ኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ እንዲሁም የዴጉና ቤጂንግ የዓለም ቻምፒዮናው አትሌት፣ በተለይ እአአ በ2012ቱ የለንደን ኦሊምፒክ ርቀቱን ያጠናቀቀበት ሁኔታ በአስር ዓመታት ከማይዘነጉ ትዝታዎች መካከል ቀዳሚው በሚል በዓለም አትሌቲክስ መመረጡ የሚታወስ ነው። አትሌቱን አስደናቂ ከሚያደርጉት ምክንያቶች መካከል አንዱ፣ በርቀቱ የዓለም ክብረወሰንን ለሶስት ጊዜያት(1:41.09፣ 1:41.01፣ 1:40.91) መስበር መቻሉ ነው። መጽሄቱ መሰል ምርጫዎችን ማካሄድ የጀመረው እአአ በ1960ዎቹ ሲሆን፣ የመጀመሪያው አሸናፊም ኒውዝላንዳዊው ፒተር ስኔል ነበር። እአአ የ1970ዎቹን ክብር ደግሞ የሶቬት ህብረት አትሌት የሆነው ቪክቶር ሳኔይቭ ነበር የወሰደው። በ1980ዎቹ አሜሪካዊው ካርል ሉዊስ ምርጥ ሲሰኝ፤ የ90ዎቹንም ሌላኛው የሃገሩ ልጅ ሚካኤል ጆሃንሰን አሸናፊ ሆኗል። እአአ ከ2000-2009 ባሉት ዓመታት ምርጥ አትሌትነት ምርጫ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ ሲሆን፤ አንበሳው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ቀዳሚ ሊሆን ችሏል። አዲስ ዘመን የካቲት 2/2012ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27019
[ { "passage": "ከባድ በሆነውና ታላቅ ጽናትን በሚጠይቀው የአትሌቲክስ ዘርፍ ማራቶን ዓለም አቀፍ ተሳትፎዋን የጀመረችው ኢትዮጵያ፤ በበርካታ ገድሎች የአትሌቲክስ ታሪኳን አድምቃለች። ከኦሊምፒክ ቀጥሎ ታላቅ ስፍራ ባለው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናም የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ያስመዘገበችው በማራቶን ነው። ሃገሪቷ ካስመዘገበቻቸው 77 ሜዳሊያዎች መካከልም 10 የሚሆኑት በማራቶን የተገኙ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል ሁለቱ ወርቅ ሲሆኑ፤ አራት ብር እና አራት ነሃስ ናቸው። የኢትዮጵያ ተሳትፎ መነሻውን እአአ\nበ1983 በፊንላንዷ ሄልሲንኪ ካደረገው የዓለም ሻምፒዮና ሲጀመር በማራቶን የብር ሜዳሊያ ነው ሰንጠረዡ የተሟሸው። በወቅቱ ኢትዮጵያዊው አትሌት ከበደ ባልቻ በአውስትራሊያዊው ሮበርት ዴ ካስቴሌ ቢቀደምም ጀርመናዊውን ዋልዴማር ሴርፒኒስኪን በማስከተል የብር\nሜዳሊያ ተሸላሚ በመሆን ነበር ውድድሩን ያጠናቀቀው። ይህ ሜዳሊያም ኢትዮጵያን በሻምፒዮናው በብቸኝነት ያስጠራ ሆኖ ነው የተጠናቀቀው። ከዚያ\nበኋላ በተካሄዱት ዓለም ሻምፒዮናዎች በዚህ ርቀት ተሳትፎ እንጂ ውጤት ሳታስመዘግብ ነበር የቆየችው። ድሉ ወደ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች እስከተመለሰበት እአአ 2001 የኤድመንተን ሻምፒዮና ድረስም ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ ቆይቷል። ኤድመንተን ላይ የ23 ዓመቱ\nወጣት አትሌት ገዛኸኝ አበራ ባልተጠበቀ መልኩ ሌሎቹን አስከትሎ በመግባት ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያውን ለሃገሩ ማስመዝገብም ችሏል። በወቅቱ የአትሌት ገዛኸኝ አበራ\nየማራቶን እና የአትሌት ደራርቱ ቱሉ የ10ሺ\nሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎች ከሌሎቹ ጋር ተደምረው ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ሁለተኛ ከዓለም ደግሞ ስድስተኛ ደረጃን እንድትይዝ አድርገዋት ነበር። ገዛኸኝ በዚህ ውድድር የወንዶች ተሳትፎ እስካሁንም ያልተደገመ ድል ሲያስመዘግብ፤ በዓለም ሻምፒዮና ታሪክ ከገዛኸኝ ባነሰ እድሜ ማራቶንን ያሸነፈ አትሌት ባለመታየቱ ባለ ድርብ ክብር አትሌት ያደርገዋል። እአአ\nበ2009 በበርሊን በተካሄደው ሻምፒዮና የበላይነቱ በኬንያዊያን አትሌቶች ቢያዝም ኢትዮጵያዊው አትሌት ጸጋዬ ከበደ ግን የነሃስ ሜዳሊያውን በማጥለቅ ለሃገሩ የርቀቱን ሦስተኛ ሜዳሊያ አጥልቋል። ይህ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በማራቶን ሁለት ሜዳሊያ ያገኘችበት ሲሆን፤ በሻምፒዮናው ተሳትፎ ሴቶች የሜዳሊያ ሰንጠረዡን የተቀላቀሉበት የመጀመሪያው ዓለም ሻምፒዮናም ነው። በውድድሩ የቻይናና የጃፓን አትሌቶችን ተከትላ በመግባት የነሃስ ሜዳሊያውን ያጠለቀችው አትሌትም አሰለፈች መርጊያ ናት። በቀጣዩ የዴጉ\nየአትሌቲክስ ዓለም ሻምፒዮና ላይም ሌላኛው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በማራቶን የሜዳሊያ ሰንጠረዡን መቀላቀል ችሏል። አትሌቱ ሁለቱን ኬንያዊያን አትሌቶች ተከትሎ በመግባቱም ነበር የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነው። በ13ኛው\nየሞስኮ ዓለም ሻምፒዮና አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ እና ታደሰ ቶላ ዩጋንዳዊውን አትሌት ተከትለው የብርና የነሃስ ሜዳሊያዎችን አስመዝግበዋል። በሴቶች የታየው ውጤታማነት ግን ለሁለት ሻምፒዮናዎች ሳይደገም ነበር የቆየው። በቤጂንጉ ሻምፒዮና አትሌት የማነ ጸጋዬ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የብር ሜዳሊያውን ሲያገኝ፤ በሴቶች በኩል ሁለተኛው ሜዳሊያ የወርቅ ሆኖ ሊመዘገብ ችሏል። የጎዳና ላይ ሯጭ አትሌት ማሬ ዲባባ በሻምፒዮናው የኬንያ እና ባህሬን አትሌቶችን በማስከተልም ነው አሸናፊ ልትሆን የቻለችው። ከሁለት ዓመታት በፊት በለንደን በተካሄደው የዓለም ሻምፒዮናም በአትሌት ታምራት ቶላ የብር ሜዳሊያ ተመዝግቧል። ኢትዮጵያ በማራቶን ካስመዘገበቻቸው 10 ሜዳሊያዎች መካከል ስምንቱ ሜዳሊያዎች በወንዶች የተመዘገቡ ናቸው። በዓለም ዓቀፍ ደረጃም ባስመዘገቧቸው ሜዳሊያዎች 4ኛ ደረጃ\nላይ ሊቀመጡ ችለዋል። ከሦስት ወራት በኋላ በኳታሯ ዶሃ አስተናጋጅነት ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለ17ኛ\nጊዜ ይካሄዳል። በዚህ ሻምፒዮና ላይም ኢትዮጵያን አትሌቶች እንደተለመደው በርቀቱ የሚሳተፉ ሲሆን፤ ቡድኑን የሚወክሉት አትሌቶችም ታውቀዋል። በሻምፒዮናው ላይ በርካታ ሃገራትን ጨምሮ ማህበሩን የወከሉት የስደተኞችና በተለያዩ ምክንያቶች ለሃገራቸው የማይሮጡ በሺዎች የሚቆጠሩ አትሌቶችም ተሳታፊዎች ይሆናሉ። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በሁለቱም ጾታዎች የማራቶን ቡድኑን ከእነ ተጠባባቂዎቻቸው አስታውቋል። ምርጫውም አትሌቶቹ ባስመዘገቡት የተሻለ ሰዓት እንዲሁም በዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ዋና ዋና ውድድሮችና የወርቅ ደረጃ በተሰጣቸው ማራቶኖች ተሳትፏቸው የተመረጡ ናቸው። በውድድሮቹ ላይ እአአ ከሴፕቴምበር 2018- ኤፕሪል 2019 ድረስ ተወዳድረው ያስመዘገቡት የተሻለ ሰዓትም በሻምፒዮናው ሃገራቸውን እንዲወክሉ ያደርጋቸዋል። በወንዶች በኩል ስድስት አትሌቶች ቡድኑን ሲቀላቀሉ፤ በቅርቡ በተካሄደው የለንደን ማራቶን ተሳትፎው የኢትዮጵያን ክብረወሰን የሰበረው እና በዓለም ሦስተኛውን ፈጣን ሰዓት ያስመዘገበው አትሌት ሞስነት ገረመው በቅድሚያ የተመረጠ አትሌት ሊሆን ችሏል። ሞስነት ቀዳሚ ለመባል የቻለው ደግሞ ባስመዘገበው 2 ሰዓት ከ02 ደቂቃ\nከ55 ሰከንድ የሆነ ምርጥ ሰዓት ነው። ባለፈው ዓመት በቺካጎ ማራቶን ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው ሞስነት፤ እአአ በ2015ቱ\nየቤጂንግ ዓለም ሻምፒዮና 10ሺ ሜትር\nሃገሩን እንደወከለ የሚታወስ ነው። በለንደኑ ማራቶን ከሞስነት ጋር በአንድ ደቂቃ ልዩነት የግሉን ፈጣን ሰዓት ማስመዘግብ የቻለው አትሌት ሙሌ ዋሲሁን ለቡድኑ በሁለተኛነት ተመርጧል። አትሌቱ ያለው ሰዓት 2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ\nከ16 ሰከንድ ሲሆን፤ እአአ በ2016 የካርዲፍ ግማሽ\nማራቶን ሻምፒዮና፤ ስምንተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው። ሌላኛው አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳም ባስመዘገበው ሰዓት ቡድኑን የተቀላቀለ ሦስተኛው አትሌት ነው። እአአ በ2013ቱ\nየሞስኮ ዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ለሃገሩ ያስመዘገበው አትሌቱ፤ ባለፈው ዓመት በተካሄደው የኒውዮርክ ማራቶን የገባበት 2 ሰዓት ከ05 ደቂቃ\nከ59 ሰከንድ የሆነ ሰዓት ተመራጭ አድርጎታል። በማራቶን ዝነኛ ከሆኑ የዓለም አትሌቶች መካከል ተጠቃሽ የሆነው ሌሊሳ፤ ከኒውዮርክ ጎዳናዎች ባሻገር በቦስተን ማራቶንም ተደጋጋሚ ድሎችን አጣጥሟል። ዘንድሮ ባደረገው አራተኛ ተሳትፎውም ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው አትሌቱ። በሴቶች በኩልም በተመሳሳይ ሦስት አትሌቶች የተመረጡ ሲሆን፤ አትሌት ሩቲ አጋ ባላት ሰዓት ቡድኑን ትመራለች። አትሌቷ ቀዳሚ ምርጫ ልትሆን የቻለችው ባለፈው ዓመት በተካሄደውና የወርቅ ደረጃ ባለው የበርሊን ማራቶን ባስመዘገበችው 2 ሰዓት ከ18ደቂቃ\nከ34 ሰከንድ የሆነ ምርጥ ሰዓቷ ነው። አትሌቷ ከወራት በፊት በተካሄደው የቶኪዮ ማራቶን 2:20:40 በሆነ ሰዓት አሸናፊ ነበረች። በዚህ ዓመቱ የዱባይ ማራቶን 2 ሰዓት 17ደቂቃ ከ41 ሰከንድ የገባችው አትሌት ወርቅነሽ ደገፉም በቡድኑ የተካተተች ሁለተኛዋ አትሌት ናት።\nበማራቶን ውድድሮች የተሻለ ውጤት ያላት አትሌቷ፤ ከዱባይ በኋላ በተካሄደው የቦስተን ማራቶን አሸንፋለች። በባለፈው ዓመቱ የዱባይ ማራቶን 2 ሰዓት ከ19ደቂቃ\nከ17ሰከንድ ያስመዘገበችው ሌላኛዋ አትሌት ሮዛ ደረጀም በሻምፒዮናው ሃገሯን እንደምትወክል አረጋግጣለች። በወንዶች በኩል በተጠባባቂነት ሦስት አትሌቶች የተያዙ ሲሆን፤ በቅርቡ በለንደኑ ማራቶን ተሳታፊ የነበረው ሹራ ኪጣታ ባለው ሰዓት ቀዳሚው ተጠባባቂ ሆኗል። ሹራ በዚህ ማራቶን 2ሰዓት ከ05ደቂቃ\nከ01ሰከንድ የሆነ ሰዓት አስመዝግቧል። በተመሳሳይ በዚህ ዓመት በተካሄደው የቶኪዮ ማራቶን ተሳትፎው 2ሰዓት ከ04 ደቂቃ\nከ48ሰከንድ በመግባት ያሸነፈው አትሌት ብርሃኑ ለገሰ ሁለተኛው ተጠባባቂ ነው። ባለፈው ዓመት የዱባይ ማራቶንን 2ሰዓት ከ04ደቂቃ\nከ06 ሰከንድ የሮጠውና በለንደኑ የዓለም ሻምፒዮና በማራቶን ብቸኛውን ሜዳሊያ ያስመዘገበው አትሌት ታምራት ቶላም በተጠባባቂነት ከተያዙ አትሌቶች መካከል ይገኛል። በቶኪዮ ማራቶን በሰከንዶች ተበላልጠው ውድድራቸውን የፈጸሙት አትሌት ሹሬ ደምሴ እና ሄለን ቶላ ደግሞ በሴቶች በኩል በተጠባባቂነት የተያዙ አትሌቶች ናቸው። ከሄልሲንኪ የጀመረው\nየኢትዮጵያ የማራቶን ድል እስከ\nዶሃ እንዲዘልቅም ዝግጅቱ\nከወዲሁ ተጀምሯል። በውድድሩ\nህግ መሰረት ለሻምፒዮናው\nየተመረጠ አትሌት ለሦስት\nወራት የማገገሚያ ጊዜ የግድ\nያስፈልገዋል። በዚህም መሰረት\nአሁን አትሌቶቹ ከውድድር\nርቀው በአሰልጣኞቻቸው ልምምድ\nበማድረግ ላይ ይገኛሉ።\nበመጪው ሐምሌ ወር በሻምፒዮናው ተሳታፊ የሚሆኑ\nአትሌቶችን ለመምረጥ በኔዘርላንድ\nሄንግሎ ከሚካሄደው የሟሟያ\nውድድር በኋላም ብሄራዊ\nቡድኑ ወደ ካምፕ\nገብቶ ልምምዱን እንደሚጀምር\nየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን\nመረጃ ያመላክታል።አዲስ ዘመን ሀምሌ 8/2011 ", "passage_id": "e1b7442d800b9ee7d781bdfcb6823f6e" }, { "passage": "በቤይጂንግ ቻይናው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የወንዶቹ ማራቶን ሩጫ ውድድር፥ ኤርትራዊው ወጣት ግርማይ ገብረሥላሴ አሸነፈ። የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ ለሀገሩ በማስገኘትም ታሪክ ሠራ። በማራቶን ውድድር ታሪክ ከዚህ ቀደም በዚህ የወጣትነት ዕድሜ ያሸነፈ አትሌት የለም። በሁለተኝነት ያጠናቀቀው ደግሞ ኢትዮጵያዊው የማነ ፀጋዬ ነው።በሌላ ዜና 50ኛው የዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር አዲሱን አመራር መርጧል። የ 82 ዓመት ዕድሜ ያላቸውን ሴኔጋላዊ ላሚን ዲያክን በመተካት የተመረጡት እንግሊዛዊው ሴባስቲያን ኮ ናቸው። ዲያክ፥ ”ዓለምአቀፉ አካል በወጣት አመራር ተተካ” ብለዋል።በዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር 103 ዓመት ታሪክ፥ ሎርድ ሴባስቲያን ኮ በፕሬዘዳንትነት ሲመረጡ ስድስተኛው ሰው ናቸው። ", "passage_id": "f0957dcd5c3d04d250fa1533eb3e9a16" }, { "passage": "የመወዳደሪያ እድሜው ገና በወጣቶች ጎራ እያለ ከእድሜ ታላላቆቹ ጋር በታላላቅ የውድድር መድረኮች ጠንካራ ተፎካካሪ መሆን የቻለው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ከዚህ ቀደም በርካታ ጊዜ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የነገው ተስፋ እንደሚሆን ተነግሯል። ዮሚፍ ይህንን በተግባር ማሳየት የቻለውም ከሁለት ዓመት በፊት የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና ፖርትላንድ ዩጂን ላይ ሦስት ሺ ሜትሩን 7፡57፡21 በሆነ ሰዓት አሸንፎ ወርቅ ሲያጠልቅ ነበር። ዮሚፍ ይህን\nድሉን በበርሚንግሃም የዓለም\nየቤት ውስጥ ቻምፒዮና\nላይ8:14.41 በሆነ\nሰዓት ማስጠበቅ ችሏል።\nበውድድሩ ላይ ያሳየው\nድንቅ ብቃትና በተፎካካሪዎቹ ላይ የወሰደው\nየበላይነት ከእድሜው አኳያ\nበቅርብ ጊዜ ውስጥ\nውጤት በጠፋበት አምስትና\nአስር ሺ ሜትር\nቀነኒሳን የሚተካበት ወቅት\nእንደተቃረበ ማሳያ ነው።\nበዚህ ውድድር ብቻም\nሳይሆን በዋናው የዓለም\nቻምፒዮናም ይህን ማሳየት\nየቻለ አትሌት በመሆኑ\nብዙዎች ተስፋ አድርገውበታል። ቁመተ ለግላጋው\nባለተሰጥኦ አትሌት በወጣቶች\nቻምፒዮና ከአፍሪካ እስከ\nዓለም ቻምፒዮና እንዲሁም\nበዳይመንድ ሊግ ውድድሮች\nከጊዜ ወደ ጊዜ\nእያሳየ የሚገኘው ድንቅ\nብቃት የነገ የኦሊምፒክ\nተስፋነቱን ያረጋግጡለታል። ዮሚፍ\nሪዮ ኦሊምፒክ ላይ\nሜዳሊያ ማጥለቅ ባይችልም\nበመድረኩ ያለውን ልምድ\nአንድ ደረጃ ከፍ\nማድረግ ችሏል። የብቃቱ\nጥግ ላይ ለመድረስ\nእየተንደረደረ በሚገኝበት በዚህ\nወቅት ከእድሜው አኳያ\nብዙ ርቀት ተጉዟል\nማለት ይቻላል። ይህ ወጣት\nአትሌት ካለፈው ወር\nአንስቶ በተለያዩ የዓለማችን\nከተሞች እየተካሄዱ በሚገኙ\nየዓለም የቤት ውስጥ\nየዙር ውድድሮችም አስደናቂ\nብቃት በማሳየት ትግሉን\nከሰዓት ጋር አድርጓል።\nከሳምንት በፊትም በዚሁ\nበቤት ውስጥ የዙር\nውድድር በአሜሪካ ሚልሮስ\nጨዋታዎች የአንድ ማይል\nየቤት ውስጥ የዓለም\nክብረወሰን ለመስበር ተቃርቦ\nበሽርፍራፊ ሰከንዶች ሳይሳካለት\nቀርቷል። የዚህ ርቀት\nየዓለም ክብረወሰን ዮሚፍ\nከመወለዱ ከስድስት ወራት\nበፊት እኤአ 1997 በሞሮኳዊው ድንቅ አትሌት\nሂቻም ኤልግሩዥ የተያዘ\nሲሆን፣ ዮሚፍ ክብረወሰኑን ለመስበር ያደረገው\nትልቅ ጥረት 3:48.46 በሆነ ሰዓት ውድድሩን\nእንዲያጠናቅቅ አስችሎታል። ይህ\nሰዓት ግን የቀድሞውን\nክብረወሰን ለመስበር በዜሮ\nነጥብ ዜሮ አንድ\nማይክሮ ሰከንድ የዘገየ\nበመሆኑ እድለኛ ሳይሆን\nቀርቷል። ዮሚፍ ለጥቂት ባለመለጠው ክብረወሰን ቁጭት ውስጥ ሆኖ በሌላኛው የቤት ውስጥ የዙር ውድድር ዛሬ በበርሚንግሃም ላይ በአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የሚያደርገው ፉክክር በጉጉት ይጠበቃል። ዮሚፍ ከሳምንት በፊት ሞክሮ ያልተሳካለት የኤልግሩዥ የማይል ክብረወሰን ቢሆንም በሳምንት ልዩነት  የኤልግሩዥን ሌላ ክብረወሰን የማሻሻል እድል ገጥሞታል። የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የቤት ውስጥ ክብረወሰን በኤልግሩዥ\n3:31.18 በሆነ ሰዓት የተያዘ ሲሆን፣ ይህን ክብረወሰን ያስመዘገበው የማይል ክብረወሰኑን ካስመዘገበ ከአስር ቀናት በኋላ ነበር። ዮሚፍ የማይል ክብረወሰኑን ባያሳካም ከኤልግሩዥ ጋር ሊጋራው የሚችል ተመሳሳይ ታሪክ ገጥሞታል። በዛሬው ውድድር ዮሚፍ\nክብረወሰን ለማሻሻል የተሻለ\nእድል እንዳለው ከተፎካካሪዎቹ ጥንካሬ አኳያ\nከወዲሁ ቅድመ ግምቶች\nእየወጡ ይገኛሉ። በዚህ\nውድድር በዘንድሮው ዓመት\nየቤት ውስጥ የዙር\nውድድሮች በተለያዩ ሦስት\nከተሞች ማሸነፍ የቻሉ\nሦስት አትሌቶች ተካተዋል።\nየመጀመሪያው ጠንካራ ተፎካካሪ\nየአስራ ዘጠኝ ዓመቱ\nኢትዮጵያዊ አትሌት ሳሙዔል\nተፈራ ሲሆን፣ ከሳምንት\nበፊት ርቀቱን ፈጣን\nበተባለለት 3:35.57 ሰዓት\nቶረን ላይ ማሸነፉ\nይታወሳል። ማድሪድ ላይ\nአሸናፊ የነበረው ቢትዌል\nቢርገን እንዲሁም ካርልሹር\nላይ ማሸነፍ የቻለው\nቪንሰንት ኪቤት በዛሬው\nውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ\nይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁ\nኬንያውያን አትሌቶች ናቸው።\nበተለይም በተመሳሳይ መድረክ ባለፈው ዓመት በዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና በርሚንግሃም ላይ በወንዶች አንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያ በማጥለቅ ክስተት የነበረው ወጣቱ አትሌት ሳሙዔል ተፈራ ከዮሚፍ ጋር የሚያደርገው ፉክክር ትልቅ ትኩረት አግኝቷል። በርቀቱ ብልጭ ድርግም የሚለውን የኢትዮጵያ ተስፋ ዳግም እንዲያንሰራራ ያደረገው ሳሙዔል ከመሆኑ አኳያ የተሰጠው ግምት ቀላል የሚባል አይደለም። በታላላቅ የውድድር መድረኮች የማናውቀው ሳሙዔል ተፈራ ድንገት ባለፈው ዓመት በቤት ውስጥ የዓለም ቻምፒዮና ልምድ ያላቸውን አትሌቶች ያሸነፈበት መንገድም ኢትዮጵያ ጠንክራ  ከሠራች\nስኬታማ እንደምትሆን ያሳየ\nነበር። ይህ አትሌት በርቀቱ እኤአ ከ2012 ቱርክ ኢስታንቡል ደረሰ መኮንን ካስመዘገበው ውጤት ወዲህ የመጀመሪያው ሲሆን፣ በዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና ወርቅ ሲያስመዘግብ ከኃይሌ ገብረስላሴና ደረሰ መኮንን ቀጥሎ ሦስተኛው አትሌት ነው። አገር አቀፍ ውድድር አሸንፎ በለንደን ቻምፒዮና ኢትዮጵያን መወከል የቻለው ሳሙዔል በወጣቶች የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና በእድሜም በልምድም ከሚበልጡት የዓለማችን ጠንካራ አትሌቶች ጋር ተፎካክሮ ማሸነፍ ብቻም ሳይሆን ከሃያ ዓመት በታች የዓለም ክብረወሰንን 3፡ 36፡05 በሆነ ሰዓት የግሉ ማድረግ የቻለ ጠንካራ አትሌት ነው። ሳሙዔል ከመነሻው አንስቶ ብቃቱን እያሳደገ በትልቅ ደረጃ ቻምፒዮን እስከመሆን የደረሰ አትሌት መሆኑ ወደ ፊትም በትልቁ የዓለም ቻምፒዮናና ኦሊምፒክ መድረኮች ትልቅ ተስፋ የሚጣልበት አትሌት መሆን ችሏል።አዲስ ዘመን የካቲት 9 ቀን 2011 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "21a94856080ad8a372ceab907f914e83" }, { "passage": "ከዓምናው የዓለም ሻምፒዮና የ10,000 ሜትር ሁለተኝነቷ በኋላ፣  ለተሰንበት ግደይ በ5,000 ሜትር የመም (ትራክ) ላይ ሩጫ የምንጊዜውም እጅግ ፈጣኗ ሴት ሆናለች። ኢትዮጵያዊቷ ለሰንበት፣ ረቡዕ ጥቅምት 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ባደረገችው አስደናቂ ሩጫ ለ12 ዓመታት በጥሩነሽ ዲባባ ተይዞ የነበረውን በስፔን ቫሌንሽያ ከተማ፣ በ14:06.62  በመሮጥ ነው የዓለምን ክብረወሰን መስበር የቻለችው። ይህ ድንቅ ክንዋኔዋ ነው በጥሩነሽ ዲባባ በ2008 በ14:11.15 ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን ለመስበር የበቃችው።ኦሊምፒክ ቻነልና ራነርስ ወርልድ እንደዘገቡት የመጨረሻዎቹን አምስት ዙሮች ብቻዋን የሮጠችው ለተሰንበት፣ ከውድድሩ ፍጻሜ በኋላ \"ይህ የረዥም ጊዜ ሕልሜ ነው፤ በውድድሩም በጣም ተደስቻለሁ!\" ብላለች።  \"ይህ በጣም ግሩም ነው፡፡ ከዚህ በፊት ጥሩነሽ ዲባባ ሰበረች፤ አሁን ደግሞ እኔ፡፡” ስትልም አክላለች። የ5,000 ሜትር የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር የኢትዮጵያውያን ሯጮች የፈጣን ሯጭነት ውርስን የ22 ዓመቷ ለተሰንበት አስቀጥላለች።ሌላው የምሽቱ ተጨማሪ  የክብረ ወሰን አስደናቂ ክስተት በቀነኒሳ በቀለ በ26:17.53  ለ15 ዓመታት ተይዞ የነበረው የ10,000 ሜትር ሪከርድን ዑጋንዳዊው ጆሹዋ ቼፕቴጊ በ26:11.02 በመፈጸም መስበሩ ነው። ባለፈው ነሐሴ በተደረገው ዳይመንድ ሊግ በ5000 ሜትርም የቀነኒሳን የዓለም ሪከርድ መስበሩም ይታወሳል፡፡", "passage_id": "d7533a78252bfbdc1d1f94a4b4fa4a46" }, { "passage": " በዓለማችን የተለያዩ ከተሞች በሚካሄዱ ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች ምስራቅ አፍሪካውያኑ ጐረቤታሞች የርቀቱ ፈርጥ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ በዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ከወርቅ እስከ ነሐስ ደረጃ ድረስ በተሰጣቸው የጐዳና ላይና የማራቶን ውድድሮች ኬንያውያንና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የዘወትር ተፎካካሪና አሸናፊዎች ቢሆኑም በዱባይ ማራቶን የኢትዮጵያውያን የበላይነት ሃያል ነው ማለት ይቻላል፡፡ለዚህም ባለፉት በርካታ ዓመታት በተካሄዱ ውድድሮች በሁለቱም ፆታ ከአንድ እስከ አስርና ከዚያ በላይ ያለውን ደረጃ ይዘው ማጠናቀቃቸው ማሳያ ነው፡፡ ይህም በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ ውድ በሆነው የማራቶን ውድድር አረንጓዴውን ጎርፍ ዘወትር እንድናየው ያስቻለ ነው። ከዚህ ባሻገር ዘወትር የፈረንጆች አዲስ ዓመት በገባ ከሁለት ሳምንት በኋላ አርብ እለት በሚካሄደው የዱባይ ማራቶን በርካታ ኢትዮጵያውያን በአረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ቀለማት አሸብርቀው የዱባይ ጎዳናዎች ድምቀት መሆናቸው የውድድሩ መለያ እስከ መሆን ደርሷል፡፡በጣት የሚቆጠሩ ቀናትን ባስቆጠረው የፈረንጆች አዲስ ዓመትም በርካታ ኢትዮጵያን አትሌቶች ለዱባይ ማራቶን እየተዘጋጁ ይገኛሉ፡፡ ለእያንዳንዱ አሸናፊ አትሌት እንደየደረጃው ከሁለት መቶ ሺ ዶላር በላይ በመሸለም የዓለማችን ከበርቴ ውድድር በሆነው የዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአሸናፊነት በተጨማሪ ፈጣን ሰዓቶችን በማስመዝገብ የውድድሩን ክብረወሰን ደጋግመው በማንሳት ይታወቃሉ። ለዚህም ባለፉት ሁለት ዓመታት በተለይም በወንዶቹ ውድድር የተመዘገቡት ሰዓቶች ምስክር ናቸው።አትሌት ታምራት ቶላ ካቻምና ውድድሩን ሲያሸንፍ ያስመዘገበው ሰዓት በማራቶን በታሪክ አስረኛው ፈጣን ሰዓት ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በሪዮ ኦሊምፒክ የአስር ሺ ሜትር የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊ የነበረው ታምራት ለጥ ባለው የዱባይ ጎዳና ፈጣኑን ፉክክር ሲያሸንፍ ያስመዘገበው ሰዓት ቀድሞ የውድድሩ ክብረወሰን ከሆነው ሁለት ደቂቃ የተሻለ ሲሆን በዚህ ውድድር የተገደበውን 2፡o4 ሰዓት መስበር የቻለ የመጀመሪያው አትሌት ያደርገዋል፡፡ አምናም ቢሆን ብዙ ትኩረት ሳይሰጠው ወደ ውድድር የገባው አትሌት ሞስነት ገረመው ይህን ክብረወሰን በሌላ የተሻለ ሰዓት የግሉ በማድረግ ማሸነፉ ይታወሳል።የውድድሩ ዳይሬክተር ኮኔርተን «በቀጣዮቹ ሳምንታት በርካታ ድንቅ አትሌቶችን ወደ ውድድሩ ለማምጣት እንጥራለን» ብለዋል፡፡\nአሰለፈች መርጊያ ሦስት ጊዜ በዱባይ ማራቶን በማሸነፍ ከሴቶች ቀዳሚ ስትሆን የጀግናውን አትሌት ሃይሌ ገብረስላሴን ክብረወሰን መጋራትም ችላለች። ሃይሌ ገብረስላሴ ከ2008 ዓ .ም ጀምሮ ለተከታታይ ሦስት ጊዜ የዱባይ ማራቶንን ያሸነፈ ብቸኛው አትሌት መሆኑ አይዘነጋም። አሰለፈች መርጊያ በ2011፤ 2012ና 2015 የዱባይ ማራቶንን ከማሸነፏም በላይ በርቀቱ የቦታው የክብረወሰን ባለቤት ነች። አሰለፈች ክብረወሰኑን ያስመዘገበችው በ2012 ባሸነፈችበት ውድድር ሲሆን ሰዓቱም 2:19:31 ሆኖ ተመዝግቧል።አንደኛ ሆኖ ያጠናቀቀ አትሌት ሁለት መቶሺ ዶላር፤ ሁለተኛው ሰማንያ ሺና ሦስተኛው አርባ ሺ ዶላር በሚያስገኘው የዱባይ ማራቶን በወንዶች ባለፉት አስራ ስድስት ዓመታት ኬንያውያን ስምንት ጊዜ ኢትዮጵያውያንም ደግሞ አስር ጊዜ አሸንፈዋል። በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድሉን ተቆጣጥረውታል ማለት ይቻላል። ባለፉት ስድስት ዓመታት የነበረውን ውጤት ብንመለከትም ኬንያውያን ማሸነፍ የቻሉት በአንዱ ብቻ ነው።2011 ላይ ድሉ የኬንያዊው ዴቪድ ባርማሳይ ቱሞ ነበር። ከእዚያ ወዲያ ያሉትን ውድድሮች ግን ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች አየለ አብሽሮ(የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር ያሸነፈ አትሌት ነው)፤ ሌሊሳ ዴሲሳና ፀጋዬ መኮንን በተከታታይ በማሸነፍ ታሪክ አላቸው።\nየሴቶቹን ውድድር በተመለከተ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተጋነነ የበላይነት አላቸው። ካለፉት አስራ ስድስት ዓመት ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አስራ ሁለቱን የግላቸው በማድረግ ዱባይ ላይ ነግሰዋል። እ.ኤ.አ በ2000፤ 2001ና 2002 ተከታታይ ዓመታት ሩሲያውያን አትሌቶች ነግሰው ነበር። ራሚሊያ ቡራንጉሎቫና አልቢ፤ኢቫኖቫና ኢሪና ፔርሚቲና የተባሉ አትሌቶች ተፈራርቀው አሸንፈዋል። ከእዚያ በኋላ ድሉ የኢትዮጵያዊቷ ለኢላ አማን ነበር። ከለኢላ ድል ተከትላ በቀጣዩ ዓመት ኬንያዊቷ ዴሊአ አሲጎ በ2006 የውድድሩ ቻምፒዮን ነበረች።ከእዚያ በኋላ ግን ውድድሩ ላለፉት ዓመታት ከኢትዮጵያውያን እጅ ወጥቶ አያውቅም። አትሌት ድርቤ ሁንዴ ከለኢላ በኋላ ድሉን ወደ ኢትዮጵያውያን የመለሰች አትሌት ነች። ከእዚያ ወዲህ አስካለ መገርሳ፤ ብርሃኔ አደሬ፤ ብዙነሽ በቀለ፤ ማሚቱ ደስካ፤ አሰለፈች መርጊያ(ሦስት ጊዜ) ትርፌ ፀጋዬና ሙሉ ሰቦቃ ውድድሩን ተፈራርቀው አሸንፈዋል።በዱባዩ ልዑል ሼክ ሐምዳን ቢን ሙሐመድ ቢን ራሺድ አል ማክቶም የበላይ ጠባቂነትና በዱባይ ስፖርት ምክር ቤት አዘጋጅነት የሚካሄደው ይህ ውድድር ከማራቶን በተጨማሪ የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድርና የአራት ኪሎ ሜትር የመዝናኛ ውድድር በእለቱ ያስተናግዳል፡፡ በዘንድሮው ውድድር የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ የማራቶን የብር ሜዳሊያ አሸናፊው ኢትዮጵያዊ አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ እንደሚወዳደር ቀደም ሲል አዘጋጆቹ ማሳወቃቸው ይታወሳል።አዲስ ዘመን ጥር 4/2011ቦጋለ አበበ", "passage_id": "f5961b209f72180e591cd3d46b658aeb" } ]
a8e0d49ce1faf5c1b27bfebb6e57bd5e
669b9a91b7de863580488379877838b8
በዜጎች ላይ ጥቃት እየፈፀሙ ባሉ ወንጀለኞች ላይ መንግሥት ጠንካራ እርምጃ ይወስዳል ተባለ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በዜጎች ላይ ጭካኔ በተሞላበት ጥቃት እየፈፀሙ ባሉ ወንጀለኞች ላይ መንግሥት ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ተናገሩ። የብሔራዊ የሰዎች መነገድ፣ ሰዎችን በሕገ ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገርና በሕገ ወጥ መንገድ ሰዎችን ወደ ውጭ አገር መላክ ወንጀል መከላከልና መቆጣጠር ብሔራዊ ምክር ቤት የ2013 ዓ.ም ዓመታዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።በመርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በዜጎች ላይ የተፈፀመው ድርጊት ጭካኔ የተሞላበት የወንጀለኞች ተግባር መሆኑን የገለፁ ሲሆን፤ በዜጎች ላይ ጥቃት እየፈፀሙ ባሉ ወንጀለኞች ላይ መንግሥት ጠንካራ እርምጃ እንደሚወሰድም ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያዊያን የሚጋሩትና የወረሱት የዳበረ እሴት ባለቤቶች መሆናቸውን የጠቀሱት አቶ ደመቀ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አንዳንዶች በዜጎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት እየፈፀሙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ይሄ ችግር ወደ የት እያመራ እንደሆነ ሁሉም ቆም ብሎ ሊያስብ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ዜጎችን እየጨፈጨፉ ባሉ ወንጀለኞች ላይ መንግሥት ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን የገለፁት አቶ ደመቀ፤ ለዚህም የተለያዩ ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ድርጊቱን ለማስቆምና ወንጀለኞችን ለማደን የሁሉም ጥረትና ትብብር የሚያስፈልግ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ዜጎችን ለነዋይ ብሎ መደለል፣ ድንበር አሻግሮ ለወንጀለኞች አሳልፎ በመስጠትና ለከፋ ችግር የማጋለጥ ተግባሩ መቀጠሉን በመጠቆምም፤ ለዚህ ችግር ውስጣዊና ውጫዊ ምክንያቶች ቢኖሩም ወንጀሉን ለመከላከልና ለማስቆም አሁንም የሁሉም ጥረትና ትብብር ያስፈልጋል በማለት ጥሪ ማስተላለፋቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡በተያያዘ ዜና፣ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመቆጣጠር እና ችግሩን ለመቅረፍ ምቹ የሆነች ሀገርን የመፍጠር ሥራ መሥራት እንደሚያስፈልግ በዚሁ መድረክ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መናገራቸውን ፋና ቢሲ ዘግቧል፡፡በዘገባው እንደተመላከተው፤ የመድረኩ አላማ በሕገወጥ መንገድ ለስደት የሚዳረጉ ዜጎችን ለመቆጣጠር እና ለችግር እንዳይጋለጡ ቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ እና ያለፉትንም መገምገም ሲሆን፤ በዚህም በ2012 እና 2013 ዓ.ም በሕገወጥ መንገድ ከሚሰደዱት በተሻለ የተመላሾች ቁጥር ከፍ ያለበት እንደነበር በመድረኩ ተነስቷል።ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ግን በቀጣይ ዜጎችን ከሕገ ወጥ ስደት ለመታደግ በሚደረገው ጥረት አገርን ለመኖር ምቹ ማድረግ እና በተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩትን ሥጋቶች ማስወገድ እንደሚያስፈልግ በመድረኩ የተነሳ ሲሆን፤ ለዚህም መንግሥት የሰላም የማረጋገጥ ሥራ ላይ አተኩሮ እየሠራ እንደሚገኝ አቶ ደመቀ ተናግረዋል።በመድረኩ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ፣ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38149
[ { "passage": "  በማይካድራ በልዩ ሃይል የተፈጸመው የጅምላ ጭፍጨፋ በፍጥነት እንዲጣራ አምነስቲ ጠየቀ ባለፈው ሁለት አመት ተኩል ገደማ በህወኃት አቀናባሪነትና ተሳትፎ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከ1500 በላይ ዜጎች በግፍ መገደላቸውን ያስታወቀው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ፤ በህወኃት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁሟል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ሰሞኑን በህወኃት ላይ እየተወሰደ ባለው እርምጃና በድርጅቱ  የወንጀል ሴራዎች ዙሪያ ባጠናከረው መረጃ መሰረት፤ ህወኃት ባለፈው ሁለት ዓመት ተኩል በተለያዩ ከባድ ወንጀሎች ውስጥ ሲሳተፍ መቆየቱ ታውቋል፡፡  መንግስት በደህንነት ተቋማቱና ሌሎች መንገዶች ባከናወነው ምርመራ፤፤ህወኃት በሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ከተከሰቱ ግጭቶች፣ አሰቃቂ የሰዎች ግድያና ጭፍጨፋ እንዲሁም የዜጎች መፈናቀል ጀርባ የህወሃት እጅ እንዳለበት ተረጋግጧል ብሏል፡፡በ2009 እና 2010 ዓ.ም ከሱማሌ ክልል በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች በማፈናቀል ብቻ ሳይሆን በክልሉ በተፈፀሙ አሰቃቂ ጭፍጨፋዎችና ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶችም ቀጥተኛ ተሳታፊ እንደነበር መግለጫው ያመለክታል፡፡  በሱማሌ ክልል ተቀስቅሶ በነበረው ሁከትና ብጥብጥ፣ እስከ-2 ሚ. የሚደርሱ ዜጎች መፈናቀላቸውን ከዚያም በኋላ በተፈጠሩ ተደጋጋሚ ሁከቶች በመቶዎች መገደላቸውና መፈናቀላቸው አይዘነጋም፡፡ ከ850 ሺህ በላይ ዜጎች የተፈናቀሉበትን የጌድዮ ጉጂ ግጭትም በማቀነባበር የህወኃት ረጅም እጅ እንዳለበት መንግስት ይፋ ባደረገው መግለጫ አስታውቋል።በተመሳሳይ፤ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ይከሰቱ ከነበሩ ግጭቶች፣ አሰቃቂ የዜጎች ግድያና ጥቃት ጀርባ የህወኃት የግጭት ነጋዴዎች ሚና የጎላ መሆኑን በምርመራ መረጋገጡን ነው የመንግስት  መለከታ፡፡ በቅርቡ በደቡብ ክልል፣ ኦሮሚያና ቤንሻንጉል ውስጥ ለተቀሰቀሰው ሁከትና ብጥብጥ እንዲሁም ለተፈጸመው አሰቃቂ  የዜጎች ግድያም የህወኃት ረዝም እጅ እንዳለበት ተረጋግጧል፡፡ ባለፈው ሁለት አመት ተኩል በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ለተፈጸሙ  ግድያዎች፣ ማፈናቀሎችና ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች በሙሉ የህወት ቡራኬና አቀናባሪነት የተከናወኑ መሆናቸውን መግለጫው ይጠቁማል፡፡ባለፈው ታህሳስ ወር ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን በመጣስ በትግራይ ክልል  ህገወጥ ምርጫ ያካሄደው ህወኃት፤ ሀገሪቱን ለመበታተንና ለማተራመስ የተለያዩ እቅዶችን ነድፎ ሲንቀሳቀስ እንደነበረ የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች መገኘታቸውም ነው የተመለከተው።ዘንድሮ በ2013 በኦሮሚያ በቤንሻንጉልና በደቡብ ክልል፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በብሔር ማንነታቸው ተለይተው በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ይታወቃል፡፡ ባለፉት ሁለት ወራት እንኳ በቤንሻንጉል ከ160 በላይ ዜጎች፣ በደቡብ ክልክ ጉራፈርዳ ከ30 በላይ እንዲሁም በኦሮሚያ ወለጋ ከ35 በላይ ዜጎች በብሔር ማንነታቸው ተለይተው በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውና በ10 ሺዎች ተፈናቅለው ለሰብአዊ ቀውስ መዳረጋቸው አይዘነጋም፡፡ በህወኃት ላይ የሚወሰደው የህግ የበላይነትን የማስከበር እርምጃ ከተጀመረ በኋላም በማይካድራ በአንድ ጀንበር በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ማንነታቸው ተለይቶ በአሰቃቂ ሁኔታ ጭፍጨፋ እንደተፈፀመባቸው መንግስት ያረጋገጠ ሲሆን አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ አምነስቲ ኢንተርናሽናልም፤በትግራይ ውስጥ በመቶዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ስለመካሄዱ ማስረጃ እንዳለው ገልጻል፡፡በቀን ሰራተኝነት ጭምር የተሰማሩ ንፁሃን በማይመለከታቸው ጉዳይ በጅምላ ስለ መጨፍጨፋቸው በቂ ማስረጃ አለኝ ያለው አምነስት፤ አፋጣኝ ምርመራ ተደርጎ የወንጀሉ ፈጻሚዎች በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ  ጠይቋል፡፡ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የአይን ዕማኞች ማነጋገሩን በተጨማሪም በሳተላይት ምልከታትም በየቦታው በርካታ አስክሬኖች ወድቀው መታየታቸውን ነው በሪፖርቱ ያመላከተው፡፡የህወኋት ልዩ ሃይል ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ሉግዲ እና ባናት በመከላከያ ሰራዊት መመታቱን ተከትሎ፣ ወደ ኋላ በማፈግፈግ፣ በነጋታጋው ህዳር 1 ቀን 2013 በማይካድራ የጅምላ ጭፍጨፋ መፈፀሙን ነው አምነስቲ ያስታወቀው፡፡የተገደሉ ሰዎች አስክሬንም ማይካድራ ከተማ ንግድ ባንክ አቅራቢያ በብዛት መገኘቱንና ድርጊቱም በህወኋት ልዩ ሃይሎች መፈፀሙን ነው አምነስቲ ያስታወቀው፡፡", "passage_id": "a0b218be1fcc81f026cda04bfe93c083" }, { "passage": "ሰሞኑን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደርና በክልሉ በሰሜን ሸዋ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች የታጠቁ ኃይሎች በሠላማዊ ዜጎች ላይ ተኩስ ከፍተው የንፁሃንን ህይዎት ቀጥፈዋል። የታጠቁት ኃይሎች የንብረት ዝርፊያም ከመፈፀ ማቸው ባሻገር የዕምነት ቤቶችን እስከማቃጠልና ዜጎችን አፍኖ እስከመውሰድ የደረሰ ሽብር የሚመስል ድርጊት መፈፀማቸውን ከዞኑ አስተዳደር ባለሥልጣናትና ከአካባቢው ነዋሪዎች የተገኘ መረጃ ያመለክታል። ጥቃቱን አስመልክቶ ክልሉን በበላይነት የሚመራው የአማራ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ በማዕከላዊ ጽህፈት ቤቱ አማካኝነት ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የፓርቲው ማዕከላዊ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ቧያለው የደረሰው የሰው ህይወትና የንብረት ጥፋት አዴፓ ማዘኑን ገልፀው፤ “የአሁኑን ጨምሮ በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ ግጭቶች የአዴፓ እና የአማራ ህዝብ አንድነት የሚያስፈራቸው ኃይሎች የፈጠሩት ሴራ ነው” ብለዋል። የቴክኒክ ቡድን ተቋቁሞ ጥናት እያደረገ በመሆኑ የጠፋውን የሰው ህይዎትና የንብረት መጠን ለማወቅ የቡድኑን ምላሽ እየተጠበቀ መሆኑን ጠቁመው፤ እየተወሰደ ያለውን የመፍትሄ እርምጃ በተመለከተም “ክልሉ ውስጥ ወንጀል ሠርተው በሌላ ክልል እንደበቃለን ብለው የሚያስቡ ካሉ ተስፋቸውን ይቁረጡ፤ ከአጐራባች ክልሎች እስከ ፌዴራል መንግሥት ድረስ ወንጀለኞችን ለመያዝ በጥምረት እየሠራን ነው” ብለዋል። የኦሮሞ ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) በበኩሉ የተከሰተውን ችግር አስመልክቶ ከትናንትና ወዲያ መግለጫ አውጥቷል። በሀገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ምህዳር ለማስፋትና ማንኛውንም አካል በነፃነት በመደራጀት የፈለገውን የፖለቲካ አጀንዳ በሠላማዊ መንገድ እንዲያራምድ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውንና በዚህም ተስፋ ሰጭ ውጤ ቶች መታየት ቢጀምሩም አንዳንድ የፖለቲካ ኃይሎች ግን ለውጡን ተጠቅመው ችግር እየፈጠሩ መሆናቸውን ኦዴፓ በመግለጫው አመላክቷል። “…ሆኖም አንዳንድ የፖለቲካ ኃይሎች ዲሞክራሲ ምህዳሩን በማስፋት የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው በሰለጠነና በሠላማዊ መንገድ የፖለቲካ አጀንዳቸውን ከማራመድ ይልቅ የብሔር ጽንፈኛ አስተሳሰብን አንግበው በመነሳት፣ ህጋዊና ሠላማዊ የፖለቲካ ትግል እንቅስቃሴን ከህገ ወጥና የግጭት መንገድ ጋር እያጣቀሱ እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ታይቷል” ብሏል መግለጫው። “ሰሞኑንም በእነዚህ ኃይሎች ቀስቃሽነት ግጭቶች መከሰታቸውና በሰው ህይወት፣ በአካልና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ይታወቃል” ያለው ኦዴፓ በግጭቱ ለጠፋው የሰው ህይወት፣ የአካል ጉዳት እና የንብረት ውድመት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል። የጥፋት ድርጊቱንም አጥብቆ አውግዟል። በህዝብ ደም የሚነግዱ የፖለቲካ ቁማርተኞች የተፈፀመው ጥፋት በየትኛውም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና ማንኛውንም ህዝብ የማይወክል መሆኑን የጠቆመው የኦዲፓ መግለጫ፤ “የግጭቱን ጠንሳሾች እና ተሳታፊዎች ለሕግ ለማቅረብ በሕግ አስከባሪ አካላት የሚደረገውን የሕግ የበላይነት የማስከበር እንቅስቃሴ እንዲሳካ ፓርቲያችን ያልተቆጠበ ድጋፍ ያደርጋል” ብሏል። ህዝብን በማስተዳደር ላይ የሚገኙት የሁለቱ ክልሎች መሪ ፓርቲዎች የጥቃት ፈፃሚውን አካል ማንነት በግልፅ ከመናገር ተቆጥበዋል። ከዚያ ይልቅ “አንድነት የሚያስፈራቸው ኃይሎች” እና “ጽንፈኛ የፖለቲካ ኃይሎች” የሚሉ የተለመዱ ግልፅነት የጎደላቸው አገላለፆችን መጠቀም መርጠዋል። በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለአዲስ ዘመን የሰጡ የተፎካካሪ ፓርቲ መሪዎች በበኩላቸው “ጥቃት ፈፃሚው አካል በግልፅ የሚታወቅ ሆኖ እያለ ማንነቱን ለመሸፋፈን መሞከር ወንጀለኛው ለሕግ እንዳይቀርብና ችግሩ ከመሰረቱ እንዳይፈታ የሚያደርግ ኃላፊነት የጎደለው አካሄድ ነው” በማለት መንግሥትን ይወቅሳሉ። የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፤ “ጥቃት አድራሾቹ እነማን እነደሆኑ እኮ ህዝብ ያውቃቸዋል፤ ጥቃቱ የደረሰባቸው አካባቢዎችና አስተዳዳሪዎች ሳይቀር ጥቃት አድራሾቹ እነማን እንደሆኑ እየገለፁ ባሉበት ሁኔታ አንዳንድ አካላት ምናምን እያሉ መሸፋፈን በእውነቱ ያሳዝናል። ስለሆነም በተለይም ክልሉን በሚመራው ፓርቲ የመንግሥት ባለሥልጣናት ዘንድ “የጥቃት ፈፃሚዎችን ማንነት ወደፊት ጥናት አድርገን እንገልፃለን” የሚለው አባባል የህዝብን ደህንነት መጠበቅ በለመቻላቸው ኃላፊነትን ለመሸሽ የሚደረግ ትግል ነው ብለዋል። እናም ህዝብ የሚያውቀውን እውነት ክዶ ወንጀለኛን ለመሸፋፈን መሞከር ህዝብን የበለጠ የሚጎዳ የተሳሳተ አካሄድ ነው። ስለሆነም መንግሥት አጉል መሸንገሉን ትቶ የህዝብን ደህንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት አለበት፤ በጥቃት ፈፃሚዎቹ ላይም የማያዳግም እርምጃ በመውሰድና ወንጀለኞቹን ለሕግ በማቅረብ በቀጣይም ህዝብ ለተመሳሳይ ጥቃት እንደማይጋለጥ ማረጋገጫ መስጠት ይገባል ብለዋል፤ ፕሮፌሰሩ። የኢትዮጵያ አገር አቀፍ ንቅናቄ ሊቀ መንበር ኢንጅነር ይልቃል በበኩላቸው “እኔም ሆንኩኝ ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያውቀው ጥቃት የደረሰበት አካባቢ ህዝብና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችም የሚናገሩት ጥቃቱን የፈፀመው የሰለጠነና የግልና የቡድን መሣሪያ የታጠቀ ኃይል በህዝብ ላይ መተኮሱን ነው” ይላሉ። ስለሆነም በመንግሥት ዘንድ “ግጭት” እየተባለ የሚገለፀው በጣም የሚያሳዝን ነው። የተደራጀና የታጠቀ ኃይል በሠላማዊ ህዝብ ላይ ተኩስ መክፈቱን ህዝቡ እየተናገረ ባለበት ሰዓት ግጭት ሲባል ማን ከማን ነው የተጋጨው? አያይዘውም “ግጭት ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላት የሚለው አገላለጽ መንግሥት በሁሉም ዘንድ ተወዳጅ ለመሆን እየተጠቀመበት የሚገኝ አደገኛ አካሄድ በመሆኑ ነው” ሲሉ በፕሮፌሰር በየነ ሃሳብ ይስማማሉ። “የመንግሥት ዋነኛ ተግባሩ የዜጎችን ደህንነት መጠበቅ በመሆኑ መንግሥት እያለ፣ መከላከያ እያለ፣ ደህንነት እያለ በዜጎች ላይ እንዲህ ዓይነት አሰቃቂ ጥቃት መፈፀሙ በጣም የሚያሳዝን ነው” ይላሉ። በመሆኑም ለችግሩ ኃላፊነት መውሰድ ያለበትም መንግሥት መሆኑን ያመላክታሉ። ወደፊት ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር መደረግ የሚገባውን ነገር በተመለከተም “መንግሥት ሁሉንም አካላት ለማስደሰት መሞከሩን ትቶ የሠላማዊ ዜጎችንና የህዝቡን ደህንነት በመጠበቅና በጽንፈኞች ላይ ደግሞ ቆራጥ እርምጃ በመውሰድ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት መቻል አለበት” በማለት የመፍትሔ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። አዲስ ዘመን መጋቢት 14 ዕትሙ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና መንግሥት ጊዜ በማራዘም ፖለቲካዊ ቀውሱን ሊወጣው እንደማይችለው ተገንዝቦ… በየአካባቢው ቁጥራቸው እየተበራከቱ የመጡትን የጎበዝ አለቆችና ታጣቂዎችን በሕግ አግባብ ሊያስታግሳቸው ይገባል ማለታቸው ይታወሳል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 3/2011በ", "passage_id": "7405a27a4d9d2a3ef37055a52723241e" }, { "passage": "በመንግሥት በኩል የሚሰጡ ምላሾች ችግር ፈቺ ባለመሆናቸው ምክንያት በንፁሃን ዜጎች ላይ የሚደርሰው ጭፍጨፋ መደጋገሙን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አስታወቀ፡፡\n“የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት ማክበር እና ማስከበር ያልቻለ መንግሥት ስለ ልማት እና ብልፅግና የማውራት የሞራል ልዕልና ሊኖረው አይችልም” ሲል መግለጫ ያወጣው ፓርቲው ከሰሞኑ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን በግፍ በተገደሉ ዜጎች የተሰማውን ሃዘን ገልጿል፡፡\nበክልሉ ላጋጠሙ ተደጋጋሚ ችግሮች የሚሰጡ ምላሾች ችግር ፈቺ አይደሉም ያለው ኢዜማ የችግሮቹ ምንጭ አካባቢውን የሚያስተዳድረው የመንግሥት መዋቅር እና ችግሩን በቸልታ እያየ ያለው የፌደራል መንግሥት ነው ብሎ እንዲያምን መገደዱን በመግለጫው አስታውቋል።\nከዚህ በፊት የተፈፀሙ ጥቃቶች አጥፊዎች እና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ አመራሮች ላይ ሕጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃዎች ባለመወሰዳቸው ችግሩ አሁንም ስለመቀጠሉም ነው የገለጸው።\nክልሉን በሚመሩት ኃላፊዎች ላይ ማጣራት ተደርጎ እርምጃ ካልተወሰደ ግድያና ማፈናቀሉ ይቆማል ብሎ እንደማያምንም በመግለጫው አስቀምጧል።\nየፌደራል መንግሥት እንደዚህ ዓይነቱ ጥቃቶች ከመድረሳቸው በፊት ለመከላከል እና በቶሎ ለማስቆም ከምንም ጉዳይ በላይ ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባልም ነው ያለው፡፡\n“የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር የዜጎችን በሕይወት መኖር ማክበር እና ማስከበር ነው” ያለም ሲሆን “ይሄን ማድረግ ያልቻለ መንግሥት ስለ ልማት እና ብልፅግና የማውራት የሞራል ልዕልና ሊኖረው” እንደማይችልም ገልጿል፡፡\nከሰሞኑ በክልሉ ተፈጸመ በተባለው ጥቃት ከ80 የሚልቁ ሰዎች ህይወት ማለፉን ያልተረጋገጡ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡\nጥቃቱ ማንነትን መሰረት አድርጎ መፈጸሙንም ነው መረጃዎች የሚያመላክቱት፡፡\nከአሁን ቀደም በአካባቢው ተደጋግመው በተፈጸሙ ጥቃቶች በርካቶች መገደላቸውና መፈናቀላቸው የሚታወስ ነው፡፡\n", "passage_id": "86b7b567bf047fb2003c38d7da2ca952" }, { "passage": "ኢሰመጉ ኃላፊነታቸውን ባለተወጡ የመንግሥት ኃላፊዎችና የፀጥታ ኃይሎችም ላይ ህጋዊ ዕርምጃ ይወሰድ ሲል ኮሚሽኑ በበኩሉ የሰሞኑ ድርጊት የህግ የበላይነትን በዕጅጉ የተፈታተነ ነው ብሎታል፡፡\n", "passage_id": "bd1cef59cef7dd55151d8ede7de9ff8d" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ሠብዓዊ መብት ኮሚሽን የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል 40 ከተሞች የተፈፀመውን የሠብዓዊ መብት ጥሰት አስመልክቶ ያዘጋጀውን ሪፖርት ይፋ አድርጓል።ኮሚሽነሩ ዶክተር ዳንኤል በቀለን ጨምሮ ሌሎች ባለሙያዎች ሪፖርቱን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች መግለጫ እየሰጡ ነው።በከተሞቹ በተደረገው ዳሰሳ 30 ሙያተኞች መሳተፋቸው ተገልጿል።የቀረበው ሪፖርት ከአርቲስቱ ግድያ ቀን ጀምሮ እስከ ሶስት ቀን የነበረውን ሁኔታ የዳሰሰ ነው።በዳሰሳው ጉዳት ከደረሰባቸው የመንግስት አካላት ለ328 ሰዎች ቃለ መጠይቅ ተደርጓል፤ የፎቶግራፍ፣ የድምፅና ሌሎችም መረጃዎችና ማስረጃዎችም ተካተዋል።በዚህም 123 ሰዎች ተገድለዋል 520 ሰዎች ደግሞ ለአካል ጉዳት ተዳርገዋል።", "passage_id": "2504d3456bd453b05ee7180b5a995030" } ]
d549feb9b9916dbb92c4c4335ec7f47e
cbe93c7208ee5934e55316e0def8fc86
“ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚናገሩት እና የሚተገብሩት አንድ ሊሆን ይገባል” ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር
ሙሉቀን ታደገ አዲስ አበባ፡- ቀጣዩን ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ለማድረግ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚናገሩት እና በተጨባጭ የሚተገብሩት አንድ አይነት ሊሆን ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ተናገሩ፡፡ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ባለው ሁኔታ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚናገሩት እና በተጨባጭ የሚተገብሩት ለየቅል ሆኖ ይታያል፡፡ ይህ ደግሞ አንዳንድ ፓርቲዎች ሲመቻቸው የሃይል አማራጭን በሌላ ጊዜ ደግሞ ሰላማዊ መስለው እንዲታዩ አድርጓቸዋል፡፡በመሆኑም ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የምርጫ ሕጉን እና የሥነ ምግባር ደንቡን አክብሮ መንቀሳቀስ ይገባቸዋል፡፡ በዚህም ከምርጫ በፊት፣ በምርጫ ጊዜ እና በደህረ ምርጫ በሀገሪቱ ማንኛውም አይነት ግጭት እንዳይከሰት ከማድረግ አንፃር ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የራሳቸውን ሚና መጫወት ይገባቸዋል፡፡ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን በመሸጥ ህዝቡን አሳምነውእንዲመረጡ ለማድረግ በምርጫ ሕጉ እና በምርጫ ሥነ ምግባሩ መሰረት ሊንቀሳቀሱ ይገባል የሚሉት ፕሮፌሰር በየነ፤ በዚህም ቀጣዩን ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሃዊ ማድርግ እንደሚቻል ጠቁመዋል።እንደ ፕሮፌሰር በየነ ገለፃ፤ ሰላማዊ ፖለቲካ የሚያራምዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀገሪቱን ሰላም የሚያናጋ እንቅስቃሴ ውስጥ አይገቡም። ምክንያቱም ሰላማዊ ፖለቲካ የሚያራምዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ሕጉ እና የምርጫ ሥነ ምግባር ደንቡን አክብረው የሚንቀሳቀሱ ናቸው። ካለፉት ዓመታት የምርጫ ልምዶቻችን መገንዘብ እንደቻልነው የምርጫ ሂደትን የሚያደፈርሱ እንቅስቃሴዎች ብዙ ጊዜ በዋነኛነት የሚስተዋለው ከገዢው ፓርቲ ከሚፈፀሙ ያልተገቡ ተፅዕኖዎች እና የምርጫ ህጉን እና የስነ ምግባር ደንቡን ባልተከተሉ የመንግሥት አካላት መሆኑን የገለፁት ፕሮፌሰር በየነ፤ አሁንም በቀጣይ ለሚደረገው ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ለማድረግ በቀበሌ እና በወረዳ ደረጃ የሚገኙ የገዢው መንግሥት ባለስልጣናት የምርጫ ህጉን እና የስነ ምግባር ደንቡን ማክበር እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል። እንደ ፕሮፌሰር በየነ ገለፃ፤ ምርጫ የሚካሄደው ከፌዴራልና ከክልል ባሻገር በቀበሌ እና በወረዳ ደረጃ ስለሆነ በቀበሌ እና በወረዳ ደረጃ ያሉ የገዢው ፓርቲ አባላት እና የመንግሥት የፖለቲካ ሥራ የሚሠሩ አካላት ከቀድሞው ከኢህአዴጋዊ መንፈስ የፀዱ ሊሆኑ ይገባል። ይህን በቀበሌ እና በወረዳ ደረጃ ያሉ ከኢህአዴጋዊ እንቅስቃሴ ያልተላቀቁ የገዢው መንግሥት የፖለቲካ ሹመኞች በምርጫ ህጉ እንዲገዙ ለማድረግ እስከ ምርጫ ባለው ጊዜ ድረስ የብልፅግና ፓርቲ ማስተካከያ ያደርጋል የሚል እምነት እንዳላቸውም ገልፀዋል።የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲም እንደ አንድ ተፎካካሪ ፓርቲ ደጋፊዎቹን እና ተከታዮቹን የምርጫ ሕጉን እና የሥነ ምግባር ደንቡን ተከትለው እንዲንቀሳቀሱ ለማድረግ ፓርቲው እየሠራ እንደሚገኝ ፕሮፌሰር በየነ አመላክተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38146
[ { "passage": " “ፓርቲዎች አሸንፈው መንግስት በመሆን ብቻ የሚያምኑ ከሆነ የፖለቲካን ሙሉ ቅርጽ አያሳይም፤ መሸነፍንም መለማመድ አለባቸው። በቤተሰብ፣ በጓደኛና በማህበር የፖለቲካ ፓርቲ መመሥረት አያዋጣም። መንግስትንና ፓርቲን፤ እንዲሁም ፓርቲንና ኢትዮጵያን አንድ አድርጎ ማየት ተገቢ አይደለም።” ይህንን የተናገሩት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሲሆኑ፤ የንግግሩ አውድ ደግሞ ሰሞኑን ከአገሪቱ ፓርላማ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡበት ወቅት ነው። ለመሆኑ የሀሳቡን አንድምታና ምልከታ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች እንዴት ያዩታል?በየካ ክፍለ ከተማ ጃን ሜዳ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት አቶ ማስተዋል መኮንን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የፖለቲካ ፓርቲዎች አሸንፈው መንግስት በመሆን ብቻ የሚያምኑ ከሆነ የፖለቲካን ሙሉ ቅርጽ አያሳይም። መሸነፍንም መለማመድ ያስፈልጋል›” ማለታቸው አዎንታዊ ሀሳብ ነው። ሀሳቡ ዓለም አቀፋዊና የዴሞክራሲ መርኅ ነው። የትኛውም የፖለቲካ ድርጅት በዋናነት መወዳደር ያለበት ለማሸነፍ ቢሆንም፤ ከዚህ ውጭ ግን በተቃራኒ ውጤት ከመጣ መሸነፍንም በጸጋ መቀበል አለበት። ይህ ካልሆነ የአገር ሠላምና የዜጎች ደኅንነት አስተማማኝ አይሆንም። ነገር ግን ይህ እንዲሆን ቅድሚያ መሠራት ያለባቸው ብዙ ጉዳዮች አሉ። እንደእርሳቸው\nማብራሪያ፤\n“አሁን\nያለው\nየምርጫ\nቦርድ\nተዓማኒ\nነው\nወይ?\nገዥው\nፓርቲ\nበምርጫ\nቦርዱ\nሥራ\nጣልቃ\nአይገባም\nወይ?”\nየሚሉና\nመሠል\nገፊ\nምክንያቶች\nመወገድ\nአለባቸው።\nእነዚህ\nሀሳቦች ካልተወገዱ ግን መሸነፍን መለማመድ አለባቸው ማለት ከቃል ንግግር የዘለለ ፋይዳ የለውም። በተለይ፤ በአፍሪካ ውስጥ እንዲህ አይነት ችግሮች የሚከሰቱት ሀሳቡን ባለመረዳት አይደለም። የመሸነፍን ጽንሰ ሀሳብ ባለመቀበልና ባለመውደድ ብቻ ሳይሆን ፍትሐዊ አይደለም የሚያስብሉ ነገሮች ስላሉ ነው። ‘ፓርቲዎች በጓደኛ፣ በቤተሰብና በማህበር መመስረት የለባቸውም’ የሚለውም ሀሳብ ትክክል ነው የሚሉት አቶ ማስተዋል፤ ነገር ግን የአገሪቷ ፖለቲካ የሰፈር ፖለቲካ በመሆኑና በሠፈር ፖለቲካ ውስጥ እየተኖረ እንዲህ አይነት የፓርቲ አደረጃጀት ትክክል አይደለም ማለቱ አጠያያቂ መሆኑን ይናገራሉ። ስለዚህ ከሥረ መሠረቱ የፖለቲካ አካሄዱ መቀየር ካልቻለ የፖለቲካ ፓርቲዎች መብዛት አይቀሬ እንደሆነም ይጠቁማሉ።አቶ ማስተዋል እንደሚሉት፤ “‘ፓርቲና መንግስት መለያየት አለበት’ የሚለውም ሀሳብም ቢሆን የሚደገፍ ነው። ነገር ግን ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለው በዚህ አይነት መንገድ አይደለም። ቀጣይነትም ያለው አይመስልም። ከአንድ መንግስት የሚጠበቀው ፓርቲና መንግስት መለያየት አለበት የሚል ቃል ሳይሆን በእርግጥም ለይቶ ማሳየት ነው።”በቦሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ጎሮ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት አቶ አንገሶም መዓሾ በበኩላቸው፤ የፖለቲካ ፓርቲን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት ሀሳብ ትክክል ነው በማለት፤ አብዛኛው የፖለቲካ ፓርቲ ለውድድር ሲቀርብ አሸንፋለሁ እንጂ ብሸነፍ በሚቀጥለው የተሻለ ተወዳዳሪ ሆኜ እመጣለሁ የሚል መርኅ ይዞ እንዳልሆነ ገልጸዋል። ፓርቲዎች ለህዝቡም ግልጽ አቋማቸውን ማሳየት እንዳለባቸው፤ የህዝቡንም ይሁኝታ ማግኘት የሚችሉት በሀሳብ ልዕልና ሲያምኑ መሆኑን ተናግረዋል። ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ብቻ ሳይሆን ገዥውም ፓርቲ ከአሁን ቀደም ከሰራቸው ስህተቶች ታርሞ በዚህ ቁመና መገኘት አለበት ሲሉም መክረዋል። እንደ አቶ አንገሶም ገለጻ፤ ፖለቲካ ፓርቲዎች ውስን የማህበረሰብ ክፍሎችን ብቻ ይዘው መንቀሳቀስ የለባቸውም። የአገሪቱ ዜጎች የፓርቲዎቹን አገራዊ ጥቅም በተመለከተ በግልጽ ማወቅም ይጠበቅባቸዋል። ከቤተሰብ፣ ከጓደኛና ከማህበር የዘለለ አባል ያልያዘ ፓርቲ ነገ ላይ ማንን እንደሚመራ አይታወቅም። ፍላጎቱና ጥቅሙም ከማህበር አይዘልም። ይልቁንም፤ ከማህበረሰቡ ጋር ተቀራርበው አስተሳሰባቸውን፣ ፕሮግራማቸውንና እቅድቸውን ግልጽ አድረገው ምህዳራቸውን በማስፋትና ብዙ አባላትን በማፍራት ሥራቸውን ማከናወን አለባቸው። ወጥ የሆነ አቋም ያለውን ፓርቲ ለማግኘትም ጊዜው የሚጠይቀውን ጥሩ የሆነ የፖለቲካ መደላደል መኖሩ የግድ ነው። “የፖለቲካ ፓርቲዎች ብዙኃኑን አሳታፊ በሆነ መንግድ መደራጀት አለባቸው፤” የምትለው ደግሞ በአራዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወጣት የሺእመቤት ቦጋለ ናት። ወጣቷ አክላም፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የማህበረሰቡን የእርስ በርስ ትስሰር ማጎልበት እንዳለባቸው በመጠቆም፤ ሁሉም በየጎራው መሮጡን ትቶ የብዙኃንን ፍላጎትና ጥቅም ማስከበር እንዳለበት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር ደግፋ ትናገራለች።“ፓርቲና አገር\nአንድ አይደለም። አገር\nሁልጊዜም ይኖራል። ህዝብ\nለአንድ ፓርቲ ይሁንታ\nካልሰጠ ማስተዳደር አይችልም።\nስለዚህ እገሌ የሚባል\nፓርቲ ከሌለ ልማት\nየለም፣ አገር የለም፣\nመበታተን ይመጣል የሚሉትን አስተሳሰቦች ወደ ጎን በመተው ፓርቲንና መንግስትን ነጣጥሎ ማየት ተገቢ ነው” በማለት ወጣት የሺመቤት አስታውቃለች።“አሁን በአገሪቷ ውስጥ ያሉት አብዛኞቹ ፓርቲዎች ተወዳድረው ሥልጣን ቢያገኙ እንኳን ምን እንደሚሰሩ አያውቁትም።” የሚሉት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ፍሮምሳ ታደሰ ናቸው። የፓርቲዎች የአባላቶቻቸው ስብጥር ከጓደኝነትና ከቤተሰብ የዘለለ መሆን እንዳለበትና አሸናፊነትን ብቻ ሳይሆን ተሸንፈውም ለአገር ሊያበረክቱ ስለሚገባቸው ጉዳይ ማወቅና ማሳወቅ እንዳለባቸውም አቶ ፍሮምሳ ይመክራሉ። አቶ ፍሮምሳ፤ ፓርቲዎች አሁን ላይ አገሪቷ ያለችበትን ሁኔታ ያለገናዘብ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆናቸውን በመጥቀስ የፓርቲዎቹ እንቅስቃሴ “በእንቀርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንደሚባለው እንዳይሆንም ስጋት እንዳላቸው አስታውቀዋል። በመሆኑም ዴሞክራሲያዊ ሁኔታዎችን ተከትለው የፖለቲካን ቅርጽ ሊያሳይ በሚችል ቁመና ላይ በመገኘት፤ በተለይ በጉርብትናና በመተዋወቅ፤ እንዲሁም መሰል የአደረጃጀት ስልቶች የሚደረገውን አካሄድ ሊከተሉ እንደማይገባ ገልጸዋል። መንግስትና ፓርቲ መለየት አለበት የሚለው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ የሚደገፈው “ፓርቲ ራሱን የቻለ አገር ባለመሆኑ ነው ያሉት አቶ ፍሮምሳ፤ ወጥ የሆነች ኢትዮጵያ ኖራ በዚህ ውስጥ በማሸነፍም፤ በመሸነፍም የሚያልፉ ፓርቲዎች ሊኖሩ እንደሚችሉና ለዚህም አገርን በማስተዳደር ሂደት ውስጥ የፓርቲን ሚና በመለየት ገዥውን ፓርቲ ጨምሮ “ከእኔ ሌላ ላሳር” የሚለውን አቋማቸውን መለወጥ እንዳለባቸው ተናግረዋል።አዲሰ ዘመን ጥቅምት 14/2012አዲሱ ገረመው", "passage_id": "c12299fe791d0f41e8ee340232478cd0" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሻለ ሀሳባቸውን በምርጫ በማቅረብ ከዴሞክራሲ እሴቶች ካፈነገጡ አካሄዶች የታረመ ተግባር ላይ ሊያተኩሩ እንደሚገባ የህግ ምሁራን ተናገሩ፡፡ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉ የህግ ምሁራን የፖለቲካ ፓርቲዎች ከሽኩቻና ከማጣጣል አባዜ የወጣ ስልጡን የምርጫ ስልትን ሊተገብሩ እንደሚገባ ተናግረዋል።በምርጫ ተሳትፏቸው ለሙግት የሚያቀርቧቸው መከራከሪያዎች ለህዝቡ አማራጭ የሚሆን ጉዳይ መሆን ይኖርበታልም ነው ያሉት፡፡የዘንድሮው ምርጫ ነጻ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲካሄድ በቅድመ ምርጫ ከፖለቲካ ፓርቲዎች የሚጠበቀው ቀዳሚ የቤት ስራም ይኸው መሆኑን አስረድተዋል።በምርጫው የያዙትን አማራጭ ሀሳብ በማቅረብና ህዝቡን አሳምኖ መመረጥ ይቻላል ብሎ ጠንካራ የሀሳብ ዝግጅት ማድረጊያ ወቅት ስለመሆኑም ይናገራሉ።አያይዘውም ካለፉት የኢትዮጵያ አፋኝና ፍትሃዊ ካልነበሩ የምርጫ ሂደቶች ትምህርትመውሰድ የግድ እንደሚሆንም ገልፀዋል፡፡ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጭምር የተሻለ የመወዳደሪያ ሜዳን በዴሞክራሲ መርሆዎች የከፈተ ነጻ ምርጫን የማካሄድ አቅም እንዳላት የምታሳይበት ሊሆን ይችላልም ነው ያሉት።ለዚህም የምርጫው መሪ ተዋንያን የሆኑት የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ ሚናቸው ጉልህ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ምሁራኑ ለምርጫው አጠቃላይ ዴሞክራሲያዊነት እና የሂደቱ ስኬታማነት መንግስት ሰላምና ደህንነት ላይ ከወዲሁ መስራት እና አማራጭ ሀሳቦች ዝግጅት ላይ በጥልቀት እንዲሰራም አጽንኦት ሰጥተዋል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል www.youtube.com/fanatelevision ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን! ", "passage_id": "e392a6878ef1b3db237d0ce524a7989a" }, { "passage": "አመራሮቹ ፓርቲው ሁለት ዓይነት የአመራር አወቃቀር አለው ብለዋል። በዚህም መሰረት የፓርቲው ሊቀ መንበር እና የፓርቲው መሪ የተለያዩ ናቸው። የፓርቲው ሊቀ መንበር የፓርቲውን የአደረጃጀትና የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ የሚመራ ሲሆን፤ የፓርቲው መሪ ፓርቲው ለፖለቲካ ስልጣን የሚያደርገውን ማንኛውም አይነት እንቅስቃሴና በመንግሥት ስልጣን ውስጥ የፓርቲውን አቋም የሚያስፈፅም አካል ነው በማለትም ያብራራሉ።\n\n• ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ የኢዜማ መሪ ሆነው ተመረጡ\n\nፓርቲው አሸንፎ ስልጣን ቢይዝ የመንግሥትን ሥልጣን እና የፖለቲካ ስልጣንን ለመለያየት ታስቦ የተዋቀረ አደረጃጀት ነው። በዚህም መሰረት የፓርቲው ሊቀ መንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ፤ የፓርቲው መሪ ደግሞ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ሆነው ተመርጠዋል። ስለፓርቲው አቋም፣ ስለቀጣዩ ሀገር አቀፍ ምርጫና ተያያዥ ጉዳዮች ከፓርቲው ምክትል መሪ አቶ አንዷለም አራጌ ጋር ቆይታ አድርገናል።\n\nየብሔር ፓለቲካ ገኖ በወጣበት በዚህ ጊዜ የዜግነት ፖለቲካን ይዛችሁ ወደፊት ለመራመድያሰባችሁት እንዴት ነው? የምትተማመኑትስ ምንድን ነው?\n\nአቶ አንዷለም አራጌ፡ በፕሮግራምና በደንብ የያዝነው እምነት አለ። ለብሔር ጉዳይ ብለን ያነሳነው ሳይሆን፤ ኢትዮጵያን ወደተሻለ አቅጣጫ ይወስዳታል ብለን የምናምነውን በዜግነት ላይ መሰረት ያደረገ ፖለቲካ ነው የምናራምደው። ይህ ደግሞ እያንዳንዱን ዜጋ ይመለከታል። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚወከልበት ነው። በእያንዳንዱ [ሰው] ቤት ውስጥ የሚገባ ነገር ነው። ሕዝቡ በተፈጥሮው ሕብረ ብሔራዊ ነው። በመልኩ፣ በአኗኗሩ፣ በባህሉ፣ በእምነቱና በሁሉ ነገር ተሰባጥሮ የሚኖር ሕዝብ ነው። ሕዝቡ ውስጥ ያለውን ነገር መልሰን ለሕዝቡ ነው የምንነግረው። ሕዝቡ ልብ ውስጥ ያለውን መልሶ መንገር አያከስርም። በቀላሉ ፍሬ ያፈራል ብዬ አስባለሁ። በብሔር ፓለቲካ የተሰማሩት ወንድሞቻችን እና እህቶቻችንም ቢሆኑ ከዚህ አስተሳሰብ ጨርሰው ይርቃሉ ብዬ አላስብም። በተለያዩ ወቅቶች የተነሱ ግጭቶች ሊያሻቅቡ ይችላሉ። ግን ውሎ አድሮ ሥራውን ሲያዩት እነሱም ወደቀናው መንገድ ይመለሳሉ ብዬ አምናለሁ።\n\nለምሳሌ ቅንጅትን ብናይ ሕዝቡን አሳምኖ፤ የሕዝቡን ድጋፍ አግኝቶ ኢህአዴግን መገዳደር ቀላል ነበር የሆነለት። አሁን ግን በተወሰነ መልኩም ቢሆን ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ ተቀባይነት አላቸው። ኢህአዴግ ይህን ያህል ተቀባይነት ያለው መሪ ባለው ሁኔታ ፓርቲውን መገዳደር ቀላል ይሆናል?\n\nአቶ አንዷለም አራጌ፡ በእርግጥ [ቀድሞና አሁን ከኢህአዴግ ጋር መፎካከር] ልዩነት አለው። ዶ/ር ዓብይ ጋር ያለው ቀናነት፣ አርቆ አሳቢነት፣ የኢትዮጵያዊነት ስሜት በኢህአዴግ ውሰጥ ከተለመደው የተለየ ነው፤ በጎ ነገር ነው። ለዛ ሁላችንም ድጋፋችንን ቸረናቸዋል። ነገር ግን ኢህአዴግ የሚከተላቸው አላማዎቹና መርሆቹ አሁንም እንደቆሙ ናቸው። ለውጡም ቢሆን ከዶክተር ዓብይ ብዙ አልወረደም። በ547ቱም ወረዳዎች የሚወዳደሩት ዶ/ር ዓብይ ብቻ አይደሉም። ዶ/ር ዓብይ የሚወከሉት በአንድ ወረዳ ላይ ነው። ሕዝቡ በየወረዳው የሚመርጣቸው ሰዎች ውድድር የሚካሄደው ኢህአዴግ በሚያቀርባቸውና እኛ [በምናቀርባቸው ተፎካካሪዎች] አላማ፣ ማንነትና ሥነ ምግባር መካከል ነው። በብዙ ቦታዎች እናሸንፋቸዋለን ብዬ አምናለሁ። አልጠራጠርም።\n\nየኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ደጋፊ ማነው? ተከታያችን ማነው ትላላችሁ?\n\nአቶ አንዷለም አራጌ፡ የኛ ደጋፊ በሕብረ ብሔራዊ አስተሳሰብ፣ በኢትዮጵያ አንድነት፣ በኢትዮጵያ ታሪክ የሚኮራው፣ አሁንም በኢትዮጵያ ተስፋ የሚያምነው አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። ኢትዮጵያውያን ሁሉ የኛ እምነት ደጋፊዎች ናቸው። እኛ የምናወራው ስለአንድ ብሔር፣ ስለአንድ ክልል ወይም... ", "passage_id": "990b818f3651c76dfb1baaac90923d01" }, { "passage": "\nባሕር ዳር፡ ጥቅምት 13/2012 ዓ.ም (አብመድ) የኢህአዴግን ውህደት በተመለከተ በውይይት ሕዝበን ሊጠቅም ወደሚችል መንገድ መግባት እንደሚገባ ምሁራን መክረዋል፡፡በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ትምህርት ክፍል መምህር አቶ ደሞዝ ካሴ እና የፖለቲካ ፍልስፍና መምህር አቶ ሰለሞን አምባው በወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ከአብመድ ጋር ባደረጉት ቆይታ የኢህአዴግ እህት እና አጋር ድርጅቶች ለመዋሃድ የጀመሩት እንቅስቃሴ ሀገሪቱ ከገባችበት የፖለቲካ ቀውስ እንድትወጣ የሚያግዝ ነው፡፡ የሀሳብ ብዝኃነት ለማስተናገድ እና አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመፍጠርም እስካሁን ካለው የኢህአዴግ አካሄድ የተሻለ ሊሆን እንደሚችል ያምናሉ፡፡ በሀገሪቱ በስፋት ለሚስተዋሉት ብሔር ተኮር ግጭቶች ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት የተሻለ አማራጭ ሊሆን እንደሚችልም ነው ምሁራኑ የተናገሩት፡፡ ", "passage_id": "ede84f320bfc8c2446b6f47db24e5d88" }, { "passage": "አንዱ ከሳሽ ሌላው ተከሳሽ የሆኑበት የአገሪቱ የፖለቲካ ሥርዓት እንዲያከትም፣ ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር፣ የመጠላለፍ ፖለቲካ እንዲወገድና አዲስ የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ትግል እንደሚያደርግ ምክክር ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ምክክር) አስታወቀ፡፡ፓርቲው ይህን አቋሙን ይፋ ያደረገው ለሦስት ቀናት በፓርቲው ማኒፌስቶ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን ውይይትና ማሻሻያ መጠናቀቅን ተከትሎ ሰኞ ነሐሴ 4 ቀን 2012 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነው፡፡ፓርቲው የዜጎችን ነፃነት ለማስከበር የሶሻል ዴሞክራሲ ርዕዮተ ዓለም የሚከተል መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን፣ በዚህ ርዕዮተ ዓለም እየተመራ ከአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታና እሴቶችን በመውሰድና በማጣመር በሚቀርፃቸው ፖሊሲዎች የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግም የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ሳሳሁልህ ከበደ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግለሰብ የዴሞክራሲና ሰብዓዊ መብት ሙሉ በሙሉ የሚከበርበት ኅብረ ብሔራዊ ኅብረተሰብ እንዲያብብ እንደሚታገል ያስታወቀው ፓርቲው፣ በዚህም መሠረት ‹‹እጅግ ውድ የሆነው የሰው ልጅ እሴት ነፃነት እንደመሆኑ በሁሉም መስክ የግለብ ነፃነት ቀዳሚ ሥፍራ ይይዛል፤›› በማለት ፓርቲው ከቡድን መብት ይልቅ ለግለሰብ መብት ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሠራ አስታውቋል፡፡ከዚህ በተጨማሪም ሁሉም ሰዎች በተፈጥሯቸው እኩል በመሆናቸው ኢትዮጵያውያን በዘር፣ በቀለም፣ በትምህርት፣ በሀብት፣ በፆታ፣ በሃይማኖት እንዲሁም በአመለካከት ላይ የተመሠረተ አድሎ ሊደረግባቸው አይገባም የሚል አቋም የሚያራምድ ፓርቲ መሆኑንም አስታውቋል፡፡አሁን ካለው ፓርላሜንታዊ የፖለቲካ ሥርዓት ይልቅ በሕዝብ ቀጥታ የሚመረጥ ፕሬዚዳንታዊ ሥርዓት ለመገንባት እንደሚታገል ያስታወቀው ፓርቲው፣ ‹‹ለአንድ ጊዜ የተመረጠ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት አገሪቱን ለአምስት ዓመታት ይመራል፣ ይህ ፕሬዚዳንት ከሁለት ጊዜ በላይ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አይወዳደርም (አይመረጥም)፤›› የሚል የፖለቲካ ፕሮግራም እንዳለውም አስታውቋል፡፡ ከጥምር ጎሳ የተወለዱ ከ43 ሚሊዮን በላይ ዜጎች እንዳሉ የሚገልጸው ፓርቲው፣ በአዲስ አበባና ሌሎች ትልልቅ ከተሞች የሚኖሩ ሕዝቦች በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውክልና የሌላቸው በመሆኑ ውክልና እንዲኖራቸው ፓርቲው እንደሚታገልም አስታውቋል፡፡ምክክር ፓርቲ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ2011 ዓ.ም. እውቅና ካገኙ ፓርቲዎች አንዱ ሲሆን፣ ፓርቲው በአገር አቀፍ ፓርቲነት የሚወዳደር እንደሆነም አስታውቋል፡፡", "passage_id": "2628b180c2d782cd88d259372758354c" } ]
24d5352ca71ea9f354c078442da43726
c57e934ef455f0c5e11129f3ed91d9ef
የስፖርት ለሁሉምና የማህበረሰብ ስፖርት እንቅስቃሴ ፌስቲቫል
የማህበረሰብ ስፖርትን «ሁሉም ሰው በስፖርት እንቅስቃሴ እንደ ፍላጎቱና ችሎታው አቅሙ በፈቀደ መጠን መሳተፍ የሚችልበት መድረክ ነው» ሲሉ የስፖርት አዋቂዎች ይገልጹታል። የተሳትፎው ሁኔታ እንደ ዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ መርህ የስፖርት መርሃ ግብር ዓላማ፤ ሰዎች በተወዳዳሪነት ለአሸናፊነት ክብር እንዲበቁ የሚያደርግ አለመሆኑንም ያስቀምጣሉ። ከዚህ ይልቅ ሰዎች በስፖርቱ እንዲዝናኑ፣ ጤንነታቸውን እንዲጠብቁ፣ አካላቸው ለእለት ተዕለት ተግባራት ዝግጁ እንዲሆን፣ በሰዎች መካከል መልካም ግንኙነት እንዲፈጠር የሚያደርግ መንፈስ እንደሆነ ብያኔ ይሰጣል። በ1990 ዓ.ም በማህበራችን ተግባራዊ የተደረገው የስፖርት ፖሊሲም ይህንኑ በመደገፍ ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባውም አስቀምጧል።ስፖርት ለሁሉ ደግሞ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግና የውድድር አጋጣሚዎችን ቀርጾ ተግባራዊ በማድረጉ አንዱና ዋነኛው አማራጭ እንደሆነ ይታመናል። በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አዘጋጅነት የሚካሄደው የስፖርት ለሁሉም የማህበረሰብ ስፖርት እንቅስቃሴ ፌስቲቫልም ይሄንኑ መሰረት በማድረግ ከሚከናወኑ የስፖርት ሁነቶች መካከል አንዱ ነው። በፌደራል መስሪያ ቤቶች መካከል በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች የሚሳተፉበት የስፖርት ለሁሉምና የማህበረሰብ ስፖርት እንቅስቃሴ ፌስቲቫል ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም በመካሄድ ላይ ይገኛል። ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ በልዩ ድምቀት የተጀመረው ፌስቲቫሉ፤ ዘንድሮ በተለየ መልኩ ዝግጅት የተደረገበትና በርካታ ቁጥር ያላቸው የፌደራል መስሪያ ቤቶች የተሳተፉበት መሆኑ ተነግሯል ። “ስፖርት ለጤንነት፣ ለወዳጅንት፣ ለሠላም፣ ለአንድነትና ለብልፅግና” በሚል መሪ ሃሳብም በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጂሎ፤ ስፖርት ለሁሉም ፌስቲቫል አካላዊና አእምሯዊ ጤንነትን ከመገንባት ባለፈ የጋራ ዓላማ ያለው ኅብረተሰብ ለመገንባት እንደሚረዳ በመክፈቻው ላይ ተናግረዋል። የብሔራዊ ስፖርት ፖሊሲው የትኩረት አቅጣጫም ኅብረተሰቡን በሚኖርበት፣ በሚሰራበትና በሚዝናናበት አካባቢ እንደ ችሎታውና ፍላጎቱ በግልና በቡድን ተሳታፊ ማድረግ ስለሆነ የስፖርት ለሁሉም ፌስቲቫል ይህን ዓላማ ይዞ በየዓመቱ እንደሚከናወንም አመልክተዋል።የስፖርት ፌስቲቫሉ የተዘጋጀው በኦሊምፒክ መርህ መሰረት ህብረተሰቡ በሚማርበት፣ በሚሰራበትና በሚኖርበት አካባቢ በስፖርት እንቅስቃሴ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ እንደሆነም የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አስታውቋል። በሌላ በኩል በመንግስት ተቋማት የሚገኙ ሠራተኞች በሚሰሩበት ቦታ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የማድረግ ግንዛቤ፣ ፍላጎትና መነሳሳት እንዲኖራቸው ያደርጋልም ተብሏል።በተለያዩ የፌደራል መስሪያ ቤቶች ሠራተኞች መካከል በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች የሚደረገው ውድድር እስከ ግንቦት 13 ቀን 2012 ዓ.ም የሚቆይ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን፤ በየስፖርት ዓይነቱ የበላይነትን ይዘው ያጠናቀቁ መስሪያ ቤቶች በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አዘጋጅነት ሀገር አቀፍ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ተሳታፊ ይሆናሉ። 1ኛው ሀገር አቀፍ የሰራተኞች ስፖርት ለሁሉም ፌስቲቫል በኦሮሚያ ክልል አስተናጋጅነት ከሰኔ 05 -14/2012 ዓ.ም በባቱ ከተማ ይካሄዳልም ተብሏል።አዲስ ዘመን የካቲት 2/2012ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27020
[ { "passage": "‹‹ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ውድድር አማራ ክልል ሻምፕዮን ያልሆነው አንድ ጊዜ ብቻ ነው›› ብለዋል አቶ ሙሉጌታ ሉሌ17ኛው የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ውድድር እና 13ኛው ባህል ፌስቲቫል በአማራ ክልል አስተናጋጅነት በደብረማርቆስ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ከስድስት የክልሎች እና ከሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ከ700 በላይ ተወዳዳሪዎች በ13 የባህል ስፖርት ዓይነቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ በውድድሩ ጋምቤላ፣ ሶማሌ እና ሀረሪ ክልሎች አልተሳተፉም፤ ሐረሪ በፀጥታ እና ጋምቤላና ሶማሌ ክልሎች ደግሞ በበጀት ችግር ነው በውድድሩ ያልተሳተፉት፡፡ውድድሩ ከተጀመረበት የካቲት 7/2012 ዓ.ም ጀምሮም በርካታ የማጣሪያ ውድድሮች ተደርገዋል፡፡ በእነዚህ ውድድሮች አማራ ክልል በሁሉም ማጣሪያዎች ለፍጻሜ ደርሷል፡፡ እስከ ትናንት የካቲት 10/2012 ዓ.ም ድረስ በተደረጉ አምስት የዋንጫ ውድድሮች አራቱን በመውሰድ በአንደኛነት እየመራ እንደሚገኝ በአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ማኅበራት ዕውቅናና ድጋፍ ዳሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሉሌ አስታውቀዋል፡፡ ዛሬ ረፋድ ላይ በሁለቱም ፆታ በተደረገ የፈረስ ጉግስ እና ሽርጥ የፍጻሜ ውድድርም አሸናፊ ሆኗል፡፡", "passage_id": "9fcb659a0810f358d4442b72945a1f38" }, { "passage": "ስፖርት አንድነት በማጠናከር ብሄራዊ ስሜትን በመገንባት ረገድ ትልቅ ሚና ያለው ማህበራዊ ክንውን እንደሆነ ይነገራል። በጥንቃቄና በተገቢው ሁኔታ መጠቀም ካልተቻለ ስፖርቱ የአንድነት ሳይሆን የልዩነት ምንጭ እንደሚሆን ብዙ ዓለም አቀፍ ልምዶች ያመላክታሉ። የስፖርቱን ሁለት አይነት ተቃርኗዊ ግብርን ከ«መድሃኒት» አጠቃቀም ጋር ተመስሎ ሊቀርብ ይችላል። መድሃኒት ለጤና ፈዋሽም ጠንቅም የመሆን ባህሪ አለው። በአግባቡና በጥንቃቄ መጠቀም ሲቻል ፈዋሽነቱ፤ አጠቃቀሙ ሲዛባና ክፍተት ሲኖረው ጠንቅ የመሆን ተቀያያሪ ባህሪን የሚላበስ መሆኑን የህክምና ሳይንሱ ይናገራል።የመድሃኒት አዳኝነት አጠቃቀሙን ተከትሎ እንደሚሰጠው ውጤት ሁሉ ፤በስፖርቱ አንድነትን ብሄራዊ ስሜትን መገንባትና ማምጣት አጠቃቀሙን መሰረት አድርጎ ነው። የስፖርቱን ይህ ሚና በሀገራችን በተለያዩ አጋጣሚዎች ተከስተው አልፈዋል። በብሄራዊ ስሜት ግንባታ ውስጥ የስፖርቱን የተለያዩ ተቃራኒ ሚናዎችን ያሳዩ በርካታ አጋጣሚዎች ዘወር ብሎ መመልከቱ አካሄድን ለማስተካከል ይረዳልና ፤ለመመልከት ወደድን። በመጀመሪያ አንድነት በመፍጠር ረገድ ያለውን ሚና እኤአ በ2013 የደቡብ አፍሪካ ዋንጫ\nትልቁ ማሳያ ይሆኗል የዋልያዎቹ ከ31 ዓመት\nበኋላ በአፍሪካ ዋንጫ መሳተፍ በእግር ኳሱ ውስጥ ብሄራዊ ስሜት ሲገነፍል ለመታዘብ ተችሏል። ኢትዮጵያዊነት ስሜት ከገባበት ሰመመን በመቀስቀስ ከዳር እስከ ዳር በአንድነት ያስፈነጠዘ ነበር። የልዩነት ነጋሪት ጉሰማውን ድምጽ የዋጠና ፤የአንድነቱን ድምጸት ያጎላም ጭምር ነበር። በአትሌቲክስ ስፖርት የተገነባው የዘመናት ብሄራዊ ስሜትን ዳግም እንዲያንሰራራ ያደረገ ትልቅ አጋጣሚ ከመሆን በተጓዳኝ ብሄራዊ መግባባት የፈጠረ ልዩ አጋጣሚ ተብሎ እንዲነገር ያስቻለም ነበር። እነዚህ ሁለት የተለያዩ አጋጣሚዎች ስፖርትን ይህን መስመር ይዞ የወንድማማችነት፣ የወዳጅነት፣ የአንድነት ማጠናከሪያ ገመድነቱን ይገልጣሉ። ስፖርትም እንደ መድሃኒት ሁሉ በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ውጤቱ የአንድነት ዋልታና ማገር ይሆናል። በተቃራኒው ደግሞ በአግባቡና በጥንቃቄ መጠቀም ካልተቻለ ስፖርት የልዩነት ምንጭ ፣ብሄራዊ ስሜትን የሚንድ ሆኖ እናገኘዋለን።የስፖርት ብሄራዊ ስሜትን የመናድ ግብሩ በዋነኛነት ስፖርቱ መሰረትን በሳተና ብሄርን መሰረት ባደረገ መልኩ ከመከወን የሚቀዳ እንደሆነ የዘርፉ አዋቂዎች ይናገራሉ። የስፖርት ሳይንስ ምሁሩ ፒተር አሊግ (Peter algi) እኤአ 2009 ባሳተመው ጆርናል የስፖርታዊ ክንውን እንዴት አንድነትን ሸርሽሮ የልዩነት ማዕከል እንደሚሆን አስፍሮታል። በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ብሄርተኛ ክለቦች መበራከት ብሄራዊ ስሜትን ወደ ፈተና የሚከቱ መሆናቸው ላይ አስፍሯል። ፒተር ስፖርትን የአንድነት ስሜት እንዲያደበዝዝ በተለየ መልኩ በቅኝ ገዢዎች ተግባራዊ መደረጉን በመግለጽ ፤ብሄርተኛ ክለቦች በአንድ ብሄር ፣ ብሄረሰብ፣ ጎሳ\nእና ዘር ተለይቶ እንዲታወቅ ብሎም እንዲደገፍ ተደርጎ የሚመሰረት የእግር ኳስ ክለብ ሲሆን በዘመነ ቅኝ ግዛት በተለይም በአፍሪካ ተስፋፍቶ የነበረ የክለብ አደረጃጀት ነው። ቅኝ ገዥዎች ስፖርትን በተለይም ደግሞ እግር ኳስን በመጠቀም የዘር እና የባህል ልዩነቶችን በአፍሪካውያን ላይ አንዲሰርጽ ለማስቻል በነገድ ላይ የሚያጠነጥኑ ቡድኖች በስራ ቦታዎች (በፋብሪካ፣በማዕድን ቁፋሮ) ላይ ያቋቁሙ ነበር። በዚህ መልኩ ክለቦችን በመመስረት የአንድ ሀገር ህዝቦችን በልዩነትና በብሄርተኝነት፣ በጎሰኝነት፣ በጎጠኝነተ ወዘተ… አስተሳሰብ እንዲወጠሩ በማድረግ ብሄራዊ ስሜታቸውን በመሸርሸር የሀብት ብዝበዛውን ያለጥያቄ ሲያከናውኑ መቆየታቸውን በዚሁ ጽሁፍ ገልጾታል። የስፖርት ሳይንስ ልሂቁ ፒተር አልጊ እንዳስቀመጠው ቅኝ ገዥዎች ስፖርትን በተለይም ደግሞ እግር ኳስን በመጠቀም የዘር እና የባህል ልዩነቶችን በአፍሪካውያን ላይ እንዲሰርጽ ለማስቻል በነገድ ላይ የሚያጠነጥኑ ቡድኖች እንዲስፋፉ በማድረግ ስፖርትን የአንድነት ጸር አድርገው መገልገላቸውን ጽፏል። በኢትዮጵያ በተለይ የእግር ኳስ ክለቦች በአብዛኛው ማለት ይቻላል ህልውናቸው ነገድንና ከተማን መሰረት ያደረጉ ናቸው። አገራችን በቀኝ ገዚዎች እጅ ላይ በታሪክ አለመውደቋ የሚነገር ቢሆንም ቅሉ የእነርሱን አስተሳሰብ በመቃኘት በእግር ኳሱ ልዩነትን በመፍጠር የሃሳብ ቅኝ ተገዢዎች በመሆን የስፖርት ሜዳዎች  የጦርነት አውድማ ሲሆኑ ታዝበናል። የብሄራዊ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በስፖርታዊ ጨዋነት ፣ የተመልካቾች ረብሻ፣ ሁከትና ብጥብጥ በኢትዮጵያ እግር ኳስ በሚል ባስጠናው ጥናት ይሄው ሃቅ መሆኑን ማረጋገጡ በስፖርት ልሂቁ ለቀረበው አመክንዮ ይደግፋል። ጥናቱ በማሳያነት እንዳቀረበው፤ቁጥራቸው ትንሽ የማይባል ስያሜ ቅጽል ስያሜ፣ አርማ፣ ዜማ ከተፈጥሯዊ አሰፋፈር ጋር ተዳብሎ በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት ከብሄር/ፖለቲካ ጋር ተያያዥነት ኖሮት እንዲቀርብ መደረጉ ጠቅሷል። በስፖርት ውስጥ ልዩነት ለመፍጠር መንገድ የሆነውን እንዲህ አይነቱን አደረጃጀትን ተመልክቶ መፍትሄ መስጠት የሚገባ መሆኑን በጥናቱ ተካቷል። በእግር ኳሱ ውስጥ ያለው አደረጃጀት በሌሎች የስፖርት አይነቶች ላይ የሚታይም ጭምር ነው።በሀገር አቀፍ ውድድር መድረኮች ለምሳሌ እንደ መላው ኢትዮጵያ፣ የባህል ስፖርቶች ውድድርና ፌስቲቫል በመሳሰሉት የውድድሮቹ ይዘት የአገሪቱን ህዝቦች በአንድ ጥላ ስር በማሰባሰብ የባህል፣ የቋንቋ፣ የልምድ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን ከስፖርቱ ባሻገር የሚያጠናክር እሳቤን ይዞ ቢጀመርም አተገባበሩ በተቃራኒው ውጤት ሲያመጣ ለመታዘብ እየተቻለ ነው። የመላውም ሆነ የባህል ፌስቲቫሎቹ በተደጋጋሚ የስፖርታዊ ጨዋነት ሰለባ ሲሆኑ ተመልክተናል። ይህም ብቻም ሳይሆን የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታ ከባለፉት አራት ዓመታት ወዲህ ለማካሄድ አዳጋች የመሆኑም ሃቅ ከዚሁ የሚቀዳ መሆኑን መጥቀስ ያስፈልጋል። በተመሳሳይም በቅርቡ ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሊካሄድ ዝግጅቱ መጠናቀቁ ተነግሮለት የነበረው የባህል ስፖርት ፌስቲቫል ለማካሄድ ምጥ የሆነ የውድድር አይነት ነው። የሁለቱ ውድድሮች ባለፉት ሶስትና ሁለት ዓመታት ላለመካሄድና መሰረዝ የነበረው ምክንያት ደግሞ ፤አገሪቱና ሰላም ባለፉት ሁለት ዓመታት ሆድና ናጫ መሆናቸውን ተከትሎ ነበር። በተለይ ደግሞ እንደ መላው የኢትዮጵያ ጨዋታዎች ፣የባህል ስፖርቶችና ፌስቲቫል ውድድር ደግሞ የነበረውን የጸጥታ ጉድለት የሚያባብሱ መሆኑን ከስጋት የመነጨ እንደሆነ እሙን ነው። ምክንያቱም የሁለቱ ስፖርታዊ ክንውኖች ያለፈ ታሪካቸው ተደጋጋሚ የሆነ የስፖርታዊ ጨዋነት ችግር ፤ያውም ከጀርባው ሌላ አጀንዳን ባነገበ መልኩ ይንጸባረቅባቸው ነበር። የውድድሮቹ በተደጋጋሚ መሰረዝ የጸጥታውን መናጋት ከማባባስ የሚታደግ መሆኑን ተከትሎ የተወሰነ ውሳኔ መሆኑን አሳማኝ ነበር። በአገሪቱ የሰላም እጦት በነበረበት በዛን ወቅት የብሄር ፖለቲካን መሰረት ያደረጉ መገፋፋቶች በግልጽ ይንጸባረቁ ነበር። በሁለቱ የስፖርታዊ ክንውኖች በተደጋጋሚ ስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል ጋር ተያይዞ የሚሰጡት አስተያየቶች እናንሳ። ውድድሮቹ የተቃኙበት መንገድ የብሄራዊ ስሜንት የሚያላላ እንጂ የሚያጠብቅ እንዳልሆነ ብዙዎች ቅሬታቸውን ያሰሙበት ጉዳይም ጭምር ነው። «መንግስት የዘረጋው ሥርዓት ኢትዮጵያዊነት ስሜት እያደበዘዘ ነው» የሚሉ ሙግቶች አይለዋል። ለዚህ ስሜት ጎልቶ ለመውጣቱ የነበሩት አስተዋጽኦዎች ተርታ የስፖርት ዘርፍ ትልቁን ድርሻ እንዳለው የፖለቲካ ምሁራን ፣የስፖርቱ ልሂቃን ፣ የኪነ\nጥበብ ሙያተኞች፣ ደራሲያን ጭምር እንደየሙያቸው ባህሪ ይሄንኑ ሃሳብ አንጸባርቀዋል። የኢትዮጵያዊነት ስሜት እንዲደበዝዝ የስፖርቱን ሚና ከገለጹት ደራሲያን መካከል ከአስር በላይ መጽሃፍትን ማሳተም የቻለው ዓለማየው ገላጋይ በ2010 ዓ.ም «መለያየት ሞት ነው «በሚለው መጽሃፍ የአገራችን ወቅታዊ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ ቁመናን በዳሰሰበት መጽሃፍ «ስፖርትና ጦርነት» በሚለው ጽሁፍ ስር በተለያዩ ሙያተኞች የተንጸባረቀውን ሃሳብ የሚሸከም ነበር። ስፖርታዊ ክንውኖች የተቃኙበት ሁኔታ ስፖርትን ለብሄራዊ ስሜት ከመጠን በላይ እንደተወሰደ መድሃኒት እንደሆነበት አስፍሮታል።አለማየው በመጽሃፉ እንዳተተው ፤ስፖርት ለጤንነት ለወዳጅነት ለሰላም የሚበጀው ስፖርቱን ማዕከል አድርጎ በክለቦች መካከል ሲካሄድ እንጂ ብሄርን መሰረት ሲያደርግ አይደለም። ብሄርን መሰረት ያደረገ ስፖርት የመለያየት ስሜትንና እኔነትን ማጎልበት መሆኑን ይኸው እያየን ነው። መቀሌዎች የአዲግራትን ንብረት ያወደሙት በስፖርት ነው። ባህርዳሮች መቀሌ ላይ የተደበደቡት በስፖርት ሰብብ ነው፤ መቀሌዎች ወልዲያ መጥተው በብጥበጥ ሳይጫወቱ የተመለሱት በስፖርት ነው፤ ፋሲል ከነማ ከመቀሌ ከተማ ጋር ጎንደር ላይ እንዳይጫወት የተሰጋው በስፖርት ሰብብ ነው። እናስ? መለያየት በስፖርት እውን አልሆነም? ስፖርት ለጦርነት አልዋለም? ብሄር ነክ ስፖርት ክብረነክ መሆኑን ለመረዳት ደግሞ የጨዋታ ዘገባ ምን እንደሚመስል ማየት ይበቃል። ኦሮሚያ ማንን አሸነፈ? ትግራይ ማንን ረመረመ ? ደቡብ ማን ላይ ሀትሪክ ሰራ? ቤኒሻንጉል ማንን በጨዋታ ሙሉ ለሙሉ በልጦ ተገኘ? አፋር ማንን ጥሎ ገባ? ሶማሌ ማንን አታለለ ሀረሪ ማን ላይ ‹‹ሎጩ›› ከተተ …ማን ላይ ምን ስሜት አሳደረ? ጊዮርጊስ ፣ ቡናን፣ ደደቢትን … እንደምንደግፈው እንዳልሆነም በመጥቀስ መጽሃፉ ይሞግታል። የባህል ስፖርትና ፌስቲቫል የውድድር ዘገባዎችም ከዚህ የራቀ አይደለም ፤በዚህ ስፖርት ውስጥ አካል የሆነው የትግል ስፖርትን ዘገባን እንመልከት፡፡ ኦሮሚያ ከ አማራ\nይታገላሉ፤ደቡብ ከ ትግራይ ይታገላሉ፤ አፋር ከሶማሌ ይታገላሉ … ይህን አይነቱን ስሜት በሚይዘው ዘገባ የስፖርቱን ድባብ በራሱ የሚቀይርና ለአንድነት ሳይሆን ለልዩነት በር ከፋች መሆኑን አለማየው በትንታኔው ተመልክቶታል።የስፖርቱ ሚና ብሄራዊ ስሜትን እንዲያሸልብ ከማድረግ በተጓዳኝ ለራስ ብሄር ብቻ ማሰብን ያስከትላል፣ ዝቅ ሲል ደግሞ ወደ ጎሳ ይወርዳል፣ ወደ አካባቢያዊ እሳቤ እያለ ግለኝነት ትልቁን ቦታ ይዞ ይታያል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በአትሌቲክስ ስፖርት በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች የአትሌቶቹ የቡድን ስሜት ማንሳት የብሄራዊ ስሜቱ የቁልቁለት ጉዞ ወደ ግለኝነት መውረዱን ያመላክታል። በብሄራዊ ቡድን ደረጃ የሚገኙት አትሌቶች የመገኛ ምንጭ ከሆኑት ከእነዚህ የውድድር መድረኮች ነው። ብሄራዊ ስሜትን አንግቦ ሳይሮጥ የኖረን አትሌት በቡድን ስሜት የታጀበ ድልን እንዲያስመዘግብ መጠበቅ የሚያዋጣ አይሆንም። የኢትዮጵያን ክብርና ስም ትናንት በአትሌቲክስ ስፖርት ይመዘገብ የነበረው ድል ለመኮሰሱ ምክንያት ተደርገው ከሚነሱ ነጥቦች አንዱ የቡድን ስራ መጥፋት መሆኑን ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ በተደጋጋሚ ሲናገር የመደመጡ ሃቅም ከዚህ እውነታ የራቀ አይደለም። በአትሌቲክስ ስፖርት ከእነ አበበ ቢቂላ፣ማሞ ወልዴ ፣ምሩጽ ይፍጠር ትውልድ፣ እስከ እን ኃይሌ ገብረስላሴ፣ አሰፋ መዝገቡ ፣ ደራርቱ ቱሉ፣\nጌጤ ዋሚ እስከነ ፤ጥሩነሽ ዲባባ፣ መሰረት ደፋር ፣ቀነኒሳ በቀለ፣ስለሺ ስህን በነበረው የትውልድ ቅብብሎሽ አትሌቲክሱ በድል ተጉዟል። የአትሌቲክሱ የድል ውጤት በቡድን ስራ ድልን የማግኘቱ ልምድ እየወረደ መምጣቱ ይነገራል። በተለይ ከእነ ቀነኒሳ በቀለ ፣ስለሺ ስህን እግር የተተካው የእነ ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ ሰለሞን ባረጋ ፣አልማዝ አያና፣ ገንዘቤ ዲባባ ትውልድ የድልን ጣዕም እንጂ የቡድንን ስራ ጣዕምን ያደበዘዘ ነበር። ለብሄራዊ ቡድን የሚመለመሉት ስፖርተኞች ከአገር ውስጥ ውድድር እንደመሆኑ፤ የብሄራዊ ስሜትን በመሸርሸር ግለኝነትን በስፋት የሚያንጸባርቅ እንደመሆኑ ይህ መሆኑ የሚያስገርም አይሆንም።በየቡድን ስራ ከመቅረት በተጓዳኝ የአትሌቶቻችን ፉክክር ከብሄራዊ ስሜት በመውረድ የእርስ በእርስ እስከመሆን መውረዱ አደጋውን ከፍ የሚያደርግ ይሆናል። እኤአ በ2018 የዳይመንድ ሊግ\nአትሌት ሰለሞን ባረጋ እና ዮሚፍ ቀጀልቻ መካከል የተፈጠረውን ክስተት ደግሞ የአትሌቶቻችን የቡድን ስራ እየተንኮታኮተ የመምጣቱን ሃቅ በግልጽ ያመላከተም ጭምር ነበር። አንዱ አንዱን ጠልፎ ጥሎ ለመሄድ ሲሞክርና፤ አጸፋው ደግሞ ቁምጣን ጎትቶ እስከማስቀረት የደረሰ የወንድማዊነት ፍቅር በዓለም ፊት የታየበት መሆኑ ወዴት እየተጓዝን ነው የሚለውን በሚገባ ያመላከተ ነበር። በአትሌቶቻችን ተረዳድቶና ተባብሮ በብሄራዊ ስሜት ባለድል የመሆንን ባህልን በግለኝነት መተካቱን የሚያንጸባርቅ ትልቅ አጋጣሚም ጭምር ነበር። ኢትዮጵያን አትሌቶች በትናንት ድላቸው ውስጥ በቡድን ስራ ድልን በመደጋገም አገራቸውን ማኩራት ችለዋል። ኢትዮጵያውያንን በደስታ እንባ አራጭተውታል፤በአገራቸው ልጆች ኩራት በማጎናጸፍ የብሄራዊ ስሜትን ከጫፍ እስከ ጫፍ እንዲቀጣጠል አድርገዋል። አሁን እየተመለከትን ያለነው ከዚህ ለየቅል መጓዙን ነው ። በመሆኑም በስፖርት\nመገንባት የተቻለው ብሄራዊ\nስሜትን ፤በስፖርቱ በራሱ\nእየተናደ መሆኑን በተለያዩ\nየቀረቡት ማሳያዎችን ቆም ብሎ\nመመልከት ያስፈልጋል። በስፖርቱ\nውስጥ እየጎላ የመጣውን\nችግር ከወዲሁ መቅረፍ\nካልተቻለ አደጋው አስከፊ\nእንደሚሆን ለቀረቡት አመክንዮች፤\nወደ የትኛው ማዕዘን\nመወሰድ እንደሚያስፈልግም በግልጽ\nያስረዱም ጭምር ናቸው። በስፖርቱ ዘርፍ\nየብሄራዊ ስሜትን ማጠናከር\nእንዲቻል የስፖርት ኮሚሽን\nበሚገባ የውድደር ይዘቱን\nመቃኘቱ በስፖርቱ ብሄራዊ\nስሜትን ማዳን ያስችላል።\nኢትዮጵያዊነት ስሜትን በማጉላት\nበውድድሮቹ አንዱ ክልል\nየሌላውን ክልል ባህልና\nእሴት አክብሮ መጓዝ\nከተቻለ አዎንታዊ ውጤት\nማምጣት ይቻላል። በመጣንበት\nመንገድ ከተጓዝን ደግሞ\nየስፖርትን ብሄራዊ ስሜት\nነጸብራቅነት በአሉታዊ እንዲሰርጽ\nማድረጉ ይቀጥላል ማለት\nነው።አዲስ ዘመን ረቡዕ ሐምሌ 10 /\n2011 ", "passage_id": "d27d8530c76d096a5ddab0ac8e19594d" }, { "passage": "በአምቦ ከተማ 16ኛው የባህል ስፖርቶች ውድድር እና 12ኛው የባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል «የባህል ስፖርት ተሳትፎአችን ለሰላምና ለአንድነታችን» በሚል መሪ ቃል በአምቦ ስታዲየም ዛሬ በይፋ ተጀመረ።የዕለቱ ፕሮግራም መከፈትን በይፋ ያበሰሩት ክብርት ዶክተር ሂሩት ካሳዉ የስፖርት ፋይዳዎች ዘርፈ ብዙ መሆናቸዉን በማስታወስ የብሔራዊ ስፖርት ፖሊሲያችን ባስቀመጠ አቅጣጫ መሠረት ህብረተሰቡን የበለጠ በባህል ስፖርቶች ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ በጥናት ላይ የተመሠሰተ ስትራቴጂዎችን ነድፎ ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በመናገር ዉድድሩና ፌስቲቫሉ በይፋ አስከፍተዋል።የአምቦ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተፈራ በዳዳ፣አና የኦሮሚያ ስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ናስር በበኩላቸው ፤አምቦ የሠላም እና የፍቅር ከተማ አንዲሁም ዉጤታማ አትሌቶችን እና ተዋቂ መዑራንን በማፍራት በመጥቀስ መልካም የቆይታ ግዜ ይሆን ዘንድ ምኞታቸውን ገልጸዋል።የኢትዮጵያ ባህል ስፓርቶች ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ሰለሞን አሰፋዉም በመቀጠል የዘንድሮዉ የባህል ስፓርቶች ፌስቲቫልና ዉድድር ዕድሜና ጾታ ሳይገድብ ህብረተሰቡን ባህል ስፖርቶች ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድድረግ በተለይ ስፖርቱ በሚፈጥርልን መልካም አጋጣሚ የአገራችን ሠላም በጋራ ለማክበርና ለማስከበር ነዉ ብለዋል።በአምቦ ከተማ በድምቀት እየተካሄደ በሚገኘው ውድድር በ13 የስፖርት አይነቶች የሚካሄድ ይሆናል ።የስፖርት አይነቶቹም ትግል፣ ገና ፣ ገበጣ፣ ፈረስ ጉግስ፣ ፈረስ ሸርጥ፣ ኮርቦ፣ ድብልቅ ኮርቦ፣ ሻህ፣ቡብ፣ ሁሩቤ ፣ ቀስት ፣ ድብልቅ ቀስት እና በባህላዊ ጨዋታዎች ይጠቀሳሉ:፡በውድድሩ አዲሰ አበባ ፣ድሬደዋ፣አማራ፣ደቡብ ብሔር ብሔረሰብ እና ህዝቦች፣ሐረሪ እና ኦሮሚያ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።በአምቦ ስታዲየም ድምቀቱን እንደጠበቀ ከካቲት 16 እስከ 24 ዓ.ም በአምቦ ከተማ የሚካሄድ ይሆናል።በዳንኤል ዘነበ\nፎቶ ሃዱሽ አብርሃ", "passage_id": "a5718585cdea3973a4b8034607dcf699" }, { "passage": "በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት ከሚዘወተሩ የስፖርት አይነቶቸ በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል ። በተለያዩ አገራት ከፍተኛ ተቀባይነትን ማግኘት የቻለው የዳርት ስፖርት መነሻው ጥንታዊቷ ግሪክ እንደሆነች የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ። በግሪክ ወታደራዊ ተቋማት ውስጥ የዳርት ስፖርት በተለየ ሁኔታ ይዘወተር ነበር። በአጭር ጊዜም በአገሪቱ የሚኖረው ሌላው ማህበረሰብ አውቆት በስፋት ወደ ማዘውተር መሸጋገሩ ይነገራል፤ የዳርት ስፖርት፡ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በስፋት ወደ መዘውተር ሊሸጋገር የቻለውም በዚህ ሂደት ውስጥ አልፎ ነው። ዳርት አካልንና አዕምሮን የሚያነቃቃ ባህሪ የተላበሰ ስፖርት ሲሆን፤ የማሰብ ችሎታን የማሳደግ አቅም ያለው መሆኑ ስፖርቱን ተወዳጅ እንዲሆን አድርጎታል። \nስፖርቱ መነሻውን ግሪክ ያድርግ እንጂ በአሁኑ ወቅት አድማሱን በማስፋት በተለያዩ አገራት በመዘውተር ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ስፖርቱ መዳረሻውን ካደረገባቸው አገራት መካከል አንዷ ናት። ስፖርቱ በአገሪቱ መዘውተር ከጀመረ ረጅም ጊዜ እንዳስቆጠረም መረጃዎች ያመላክታሉ። የስፖርቱ መዘውተር የጀመረበት ዓመታትን ያስቆጠረ ቢሆንም በሚፈለገው የዕድገት ደረጃ ላይ እንደማይገኝ ይስተዋላል። ስፖርቱ ዕድሜ፣ ጾታ፣ ሃይማኖት፣ የዘርና ቀለም ልዩነት ሣይገድበው ማንኛውም ሰው አካሉንና አዕምሮውን ለማዳበር፤ ጤናውን ለመጠበቅ፣ በመስኩም ተወዳዳሪ ለመሆን የሚሳተፍበት ስፖርት ቢሆንም፤ በሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች እየተዝወተረ እንደማይገኝ ለስፖርቱ ቅርብ የሆኑ ሰዎች ወቀሳ ሲሰነዝሩ ይስተዋላል። ለዳርት ስፖርት እንደሌሎች የስፖርት አይነቶች ትኩረት አለመሰጠቱም ምክንያት ተደርጎ ይነሳል። \nየኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን ጽፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጥላሁን አላምረው፤ ስፖርቱ በሚፈለገው ደረጃ እንዳያድግ ከበጀት እጥረት ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውን ይናገራሉ። ይህም ስፖርቱን በብዙ መልኩ ጎድቶታል። የኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን የዓለም አቀፍ ዳርት ፌዴሬሽን (WDF) አባል መሆኑን ተከትሎ እ.ኤ.አ በ2017 በጃፓን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ኢትዮጵያ የመሳተፍ ዕድሉን አግኝታ ነበር። ለአገራችን የዳርት ስፖርት ይህ አጋጣሚ ትልቅ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ባለበት የበጀት ውስንነት ምክንያት ብሔራዊ ቡድኑን በዚህ መድረክ ላይ ለማሳተፍ ሳይቻል መቅረቱን እንደ ማሳያ ያስቀምጣሉ። \nበአገሪቱ የዳርት ስፖርት በሚፈለገው ደረጃ እንዳይጓዝ የተለያዩ ፈተናዎች እንቅፋት ቢሆኑበትም፤ ፌዴሬሽኑ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየሠራ መሆኑን አቶ ጥላሁን ያነሳሉ። ስፖርቱን ከማስተዋወቅ፣ ከማስፋፋት አኳያ በርካታ ሥራዎችን በተለየ መልኩ በማከናወን ውጤታማ መሆንም እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ለዚህም በአገር አቀፍ ደረጃ የውድድር መድረኮችን እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አማራጭ ተደርጎ እንደተወሰደም ያመለክታሉ። ለአብነትም በኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን አማካኝነት የሚዘጋጀው አገር አቀፍ የዳርት ቻምፒዮና ስፖርቱ በህብረተሰቡ ዘንድ ተወዳጅና ተዘውታሪ እንዲሆን ባለፉት ዓመታት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። \nበአገር አቀፍ ደረጃ፣ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የሚሳተፉበት ዓመታዊ የዳርት ቻምፒዮና ስፖርቱን ከማስተዋወቅ፣ ተወዳጅና ተዘወታሪ ከማድረግ ባሻገር ታዋቂ ስፖርተኞችን ከማፍራት አኳያ አበረታች ውጤትም ማግኘት መቻሉን አብራርተዋል። የውድድር መድረኩ ለስፖርቱ ውጤታማነት ያለውን አስተዋጽኦ ለመጨመር በዘንድሮው ዓመትም ቻምፒዮናው የሚቀጥል ይሆናል። የኢትዮጵያ ዳርት ቻምፒዮና ለ14ኛ ጊዜ በመጪው ሰኔ በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ ለማካሄድ ዝግጅት\n ሲደረግ የቆየ ሲሆን፤ በዓለም ዓቀፍ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ሻምፒዮናው ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ነው ያመላከቱት። \nብሔራዊ ፌዴሬሽኑ የስፖርቱን እንቅስቃሴ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንዲህ አይነት ውድድሮችን በማዘጋጀት የሚወሰን አለመሆኑን ያነሳሉ። በማንኛውም ደረጃ የሚካሄዱ የዳርት ውድድሮች፣ ግጥሚያዎችና ጨዋታዎች ወጥ በሆነ መንገድ የሚመሩት ሥራዓቶችን በማበጀት እየተሰራ ይገኛል። ስፖርቱን ትክክለኛውን መስመር እንዲይዝ የሚያደርገውን ማንዋሉ በዘርፉ ባለሙያዎች በተዘጋጀና ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎችን ባካተተ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑ ውጤቱ የተሻለ እንዲሆን ያደርገዋል ሲሉ አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ ስፖርቱ ተወዳጅ ቢሆንም፤ እየተኬደበት ያለው መንገድ መሰናክል የበዛበት መሆኑን በመጨረሻ ያነሱት፤ ኃላፊው፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኑም በቀጣይ የውድድር አማራጮችን መፍጠር ያስፈልጋል። በመሆኑም የዳርት ስፖርትን የበለጠ ተወዳጅና ተዘውታሪ ከማድረግ፣ ከማዘመን፣ ስፖርታዊ ጨዋነትን ከማስፈን፣ የመረጃ አያያዝ ሥርዓትን ከማቀላጠፍ፣ በክልል ፌዴሬሽኖች፣ ማህበራትና ሌሎች ክበባት መካከል የጋራ ግንዛቤን ከማዳበር አንፃር ሰፊ ሥራዎቸን ለመሥራት ዕቅድ መያዙን አስታውቀዋል። የዓለምን ህዝብ ሥጋት ውስጥ የከተተው የኮሮና ቫይረስን በመቆጣጠር በሀገራችን መደበኛ እንቅስቃሴ መጀመር ሲቻል ፌዴሬሽኑ እነዚህና መሰል ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሠራ በማስገንዘብ ሐሳበቸውን ቋጭተዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 13/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "c7490cbc30ca4cde47f18370fb5ddfa6" }, { "passage": " ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ በሳን ሆዜ - ካሊፎርኒያ ሲካሄድ የሰነበተው በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያዊያን የስፖርትና የባሕል ፌስቲቫል ከትናንት በስተያ ቅዳሜ ተጠናቅቋል፡፡የዓመቱ የክለቦች ደረጃዎችም ታውቀዋል፡፡የቨርጂነያ ቡድን በኔልሰን ማንዴላ ስም የተሰየመውን ዋንጫ አሸንፏል፡፡ለዝርዝሩ የተያያዘውን የአዲሱ አበበን ዘገባ ያዳምጡ፡፡", "passage_id": "6ff703d78fbc9238ca19e19ac5da8229" } ]
6393a71abe633aaf31af60c20039247e
206c97d4656a506cfc55d25c16194439
ከተሞች ለቅርጫት ኳስ ያላቸውን ግምት ትዝብት ላይ የጣሉበት ውድድር
የቅርጫት ኳስ ስፖርት በዓለማችን ላይ ተወዳጅ ከሆኑ ስፖርቶች መካከል በቀዳሚነት ይቀመጣል። በአገራችንም ቢሆን የቅርጫት ኳስ ስፖርት ጥሩ እንቅስቃሴ የሚደረግበትና በተለይም በከተሞችና ትምህርት ቤቶች አካባቢ በወጣቶች እጅግ ተወዳጅ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ስፖርቱን ለማስፋፋትና ለማሳደግ ሰፊ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን የቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በአገር አቀፍ ደረጃ እንዲካሄድ ማድረጉ አንዱ ትልቅ እርምጃ ነው። ከዚህ ጎን ለጎን ስፖርቱ ሰፊ መሰረት ያለው በከተሞች አካባቢ እንደመሆኑ ከሰባት ዓመት በፊት የከተሞች የቅርጫት ኳስ ውድድርን በየዓመቱ በማካሄድ አበረታች እርምጃ ወስዷል። ፌዴሬሽኑ ዘንድሮም የከተሞችን የቅርጫት ኳስ ውድድር ከኦሮሚያ ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመተባበር በቢሾፍቱ ከተማ እንዲካሄድ አድርጓል። ለአምስት ተከታታይ ቀናት ተካሂዶ ባለፈው አርብ በተጠናቀቀው የከተሞች የቅርጫት ኳስ ውድድር በወንዶች መካከል በሚደረገው ፉክክር አዘጋጁ ቢሾፍቱ ከተማን ጨምሮ አዳማ፣ድሬዳዋ፣ሐረሪ፣ቡታጅራ ከተሞች እንዲሁም የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ተሳታፊ ሆነውበታል። በሴቶች መካከል በሚደረገው ፉክክር ግን ባልተጠበቀ መልኩ አሰላ ከተማና የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ብቻ ተሳታፊ ሆነዋል። ከመሐል አገር ራቅ ያሉ ከተሞች በውድድሩ ለመሳተፍ ያሳዩትን ተነሳሽነት ያህል በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኙ ከተሞች በፉክክሩ ላይ መገኘት አለመቻላቸው ከበጀት እጥረት ጋር ተያይዞ መሆኑ የአገራችን ከተሞች ለስፖርቱ እየሰጡት ያለውን ትኩረት ትዝብት ላይ የጣለ ነው። አንዳንድ ከተሞች በውድድሩ መሳተፍ ያልቻሉት የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን በሚያዘጋጀው የቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ላይ ተሳታፊ በመሆናቸው ሲሆን ራቅ ያሉት ከተሞች በአገራችን ከሚታየው የፀጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ ምክኒያት እንደሆነ የፌዴሬሽኑ የስራ ሂደት ዳይሬክተር አቶ ይመር ሃይሌ ለአዲስ ዘመን ገልፀዋል።በዚህ ውድድር አግራሞትን ካጫሩት ሁነቶች መካከል የአዲስ አበባ ከተማ አፍንጫው ስር በምትገኘው ቢሾፍቱ ከተማ በሚካሄድ ውድድር በወንዶችም በሴቶችም መሳተፍ አለመቻሉ ነው። ከተማውን በሁለቱም ፆታ ወክለው ለመወዳደር ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩት ወጣቶች ከበጀት እጥረት ጋር በተያያዘ መጨረሻ ሰዓት ላይ መሳተፍ እንዳልቻሉ ከተለያዩ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። አዲስ አበባ በየወረዳው እንኳ መሳተፍ የሚያስችል እምቅና ሀይል ያለው መሆኑ ይታወቃል። በየትምህርት ቤቶችና በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ያለውን የአዲስ አበባ የወጣቶች ቅርጫት ኳስ ፍቅርና አቅምን አሰባስቦ አለመሳተፉ አሳፋሪ ነው። በአገራችን ከሚገኙ ከተሞች ሁሉ በአፍሪካ ደረጃ ለሚካሄዱ ውድድሮች ጠንካራ ቡድን መገንባት የሚያስችል የቅርጫት ኳስ ፍቅር፣ ጉልበት፣ የፋይናንስና የተጫዋቾች አቅም ያለው የአዲስ አበባ ከተማ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ነገር ግን በዚህ የወጣቶችን ችሎታ፣ አቅምና ጉልበት ለማወቅና ጠንካራ ቡድንን ለመገንባት የሚረዳ የከተሞች ውድድር ላይ አዲስ አበባ ለማሸነፍ ወይም ለመወዳደር ለምን እንዳልቻለ፣ ወይም እንዳልፈለገ የሚመለከተው አካል ትኩረት ሰጥቶት ማስተካከል መቻል እንዳለበት የብዙዎች እምነት ነው።አዲስ አበባ የአፍሪካና የኢትዮጵያ መዲና ናት። ወጣቶች፣ ታዳጊዎችና ህጻናት በስፖርት እንዲሳተፉ እድል በመስጠት በስነልቦናና በአካል ብቃት የዳበረ ትውልድ መገንባት፣ በአገር ደረጃ ትውልድን ከሱስና አልባሌ ስፍራ ማራቅ ብቻም ሳይሆን ከተሞቻችንንና ትውልድን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማስቻል ግዴታ እንጂ ውዴታ አይደለም። አዲስ አበባ በበጀት እጥረት በውድድሩ አለመሳተፉ የማይመስል ነገር ነው። የከተማ አስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን የቅርጫት ኳስ ውድድሩ ከተጠናቀቀ አንድ ቀን በኋላ እዚያው ቢሾፍቱ ላይ በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ የስፖርት ማህበራት አመራሮችን ለሁለት ቀን ሰብስቦ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሲሰጥ ነበር። በዚህ ስልጠና ላይ ሰላሳ አምስት ከሚጠጉ የስፖርት ማህበራት የተውጣጡ በመቶዎች የሚቆጠሩ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል። ለዚህም የሁለት ቀን ስልጠና ከተማ አስተዳደሩ በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ወጪ ማድረጉ አይቀሬ ነው። ጥያቄው ከተማ አስተዳደሩ በስሩ የሚገኙ የስፖርት ማህበራት አመራሮችን አያሰልጥን ሳይሆን ቅድሚያ ለየትኛው መስጠት አለበት ይሆናል። በቅርጫት ኳስ ውድድሩ በሁለቱም ፆታ ለመሳተፍ ቢበዛ ሃያ የሚሆን ተጫዋችና የልዑካን ቡድን ነው የሚያስፈልገው። የበጀት እጥረት ቢኖር እንኳን ውድድሩ በቅርብ ርቀት እንደመካሄዱ ተጫዋቾች እየተመላለሱ እንዲሳተፉ ማድረግ ቀላሉ አማራጭ ነበር። የከተማ አስተዳደሩ የስፖርት ኮሚሽነር አቶ ዮናስ አረጋይ በአመራሮቹ ስልጠና ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ‹‹ የአዲስ አበባን የስፖርት ማዕከልነት መልሰን እንገነባለን›› ሲሉ ተደምጠዋል። የከተማዋን የስፖርት ማዕከልነትና ገፅታ መገንባት ከተማዋ በስፖርቱ ያላትን ትልቅ አቅም አውጥታ በማሳየት እንደ ቅርጫት ኳስ ውድድሩ ባሉ አገር አቀፍ መድረኮች ተሳታፊ በመሆንና ቅድሚያ ለሚሰጠው ቅድሚያ በመስጠት እንደሚጀምር ሌሎቹም ቢሆኑ ሊማሩበት ይገባል። አዲስ ዘመን የካቲት 3/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=27070
[ { "passage": "የስፖርት ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው በእጅጉ እየጨመረ እንደመጣ ይታወቃል። የዓለም አገራት የስፖርት ሴክተሩን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመረዳት ብቻ የሚቆሙ እንዳልሆኑ በዘርፉ ያስመዘገቡት ውጤት ማሳያ ነው። በዓለማችን በበርካታ አገራት ከሌሎች ሴክተሮች ባልተናነሰ መልኩ ለስፖርት ልማቱ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ ስማቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ከማድረግ አልፈው ብዙ ማትረፍ ችለዋል፡፡ ለስፖርት ሴክተሩ ትልቅ ትኩረት መስጠት በማህበራዊ ፋይዳው አምራችና ጤናማ ዜጋን በማፍራት\nረገድ ያለውን ውጤት ከመረዳት ይመነጫል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ትላልቅ ውድድሮች በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ከሚገኘው ድል ጀርባ\nለአገር ፖለቲካዊ ትርፍ ማጣጣም ማስቻሉንም መታዘብ ይቻላል፡፡ ስፖርተኞች ከውድድር ድል በኋላ የሚያገኙት ረብጣ የሽልማት ገንዘብና\nየአገር ኢኮኖሚን በማንቀሳቀስ የሚገኘው ትርፍም ቀላል አይደለም፡፡ የስፖርቱን ዘርፈ ብዙ ፋይዳን በጥልቅ በመረዳት የስኬት ማማ\nላይ የወጡ እንደ ጀርመን ያሉ አገራትን ማንሳት ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለስፖርት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ረገድ ጀርመን\nበግንባር ቀደምነት ተጠቃሽ ናት። ይህች አገር ስፖርቱ በጠንካራ የፋይናንስ መሠረት ላይ ማቆም መቻሏ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ መሠረቱን\nሳይለቅ መጓዝ የቻለ አደረጃጀት መፍጠሯ ለስኬቷ ምክንያት ተደርጎ ይነሳል፡፡ የጀርመን መንግሥት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ከሚያፈስባቸው\nዘርፎች ዋነኛው ስፖርት ሊሆን የቻለውም ለዚህ ነው፡፡ ስፖርት በጀርመን ኢኮኖሚ ውስጥ 2 ነጥብ 2 በመቶ ድርሻ ይይዛል። ስፖርቱን በፋይናንስ\nአቅም እንዲጎለብት ከማድረግ በተጓዳኝ፤ ጠንካራ አደረጃጀት የተዘረጋለት ነው። በጀርመን የስፖርት ዘርፍ ይህን መልክ መላበሱ ከዘርፉ\nየሚገኘው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲጎላ ማድረጉ ይነሳል። በኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረትና ውጤት\nከሌሎች አገራት አንጻር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ በቀደሙት ጥቂት ዓመታት ለስፖርቱ ቅርብ ከሆኑ ሰዎች፣ ከመንግሥትና ከሌሎች\nባለድርሻ አካላት በኩል ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ተገቢ ትኩረት መስጠቷ ይነገራል፡፡ ለስፖርት ዘርፍ በተገቢው ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት\nእየተሰራ አለመሆኑንና የዘርፉ እድገት በቁልቁለት ጉዞ ውስጥ መሆኑም በሌላ ወገን ይነሳል። የስፖርት ሴክተሩ ውጤት አልባ መሆኑ\nግን ሁለቱንም ወገኖች እንደሚያስማማ ለመታዘብ ይቻላል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህም በመንግሥት ደረጃ ይኸው እውነታ ታምኖበት እየተሰራ\nስለመሆኑ በተደጋጋሚ እየተነገረ ይገኛል። በኢፌዴሪ ስፖርት\nኮሚሽን የዕቅድ በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እንድሪስ አብዱ፤ በአገሪቱ ባለፉት ሁለት የዕድገትና\nትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመናት ዘርፉ ለአገሪቱ ማበርከት ካለበት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጠቀሜታዎች አንፃር በሚፈለገው\nደረጃ ላይ አለመገኘቱና ውጤቱም በመላ አገሪቱ ተደራሽነት ላይ ክፍተቶች መኖራቸው እንደታመነበት ይናገራሉ:: ለዚህም የስፖርት ሴክተሩን\nመሠረታዊ ችግር በተረዳ መልኩ የ10 ዓመት የስፖርት ሴክተር ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እንዲሆን በኮሚሽኑ በኩል እንቅስቃሴ\nከተጀመረ መሰንበቱን ያስረዳሉ፡፡ ስፖርቱን ወደፊት\nለማራመድ እንቅፋት ከሆኑ መሠረታዊ ምክንያቶች መካከል በዋነኛነት ከአደረ ጃጀት፣ ከፋይናንስ፣ ከሰው ኃይል ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች\nመሆናቸውን የጠቆሙት የኮሚሽኑ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ እንየው አሊ፤ የ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ የተጠቀሱትን\nክፍተቶች በጥናት እንዲመልስ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ያስቀምጣሉ፡፡ ስትራቴጂክ ዕቅዱ አገራዊ የስፖርት ሪፎርምን መነሻ በማድረግ\nበስፋት የተዘጋጀ መሆኑንም ይገልፃሉ። በመሆኑም በአገሪቷ ቀጣይ የስፖርት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ለውጥና ውጤት ማምጣት እንደሚያስችል\nታምኖበታል፡፡ የስፖርት ሴክተሩ ሪፎርም ፕሮግራም ዘርፍን መለወጥ የሚችሉ ብዙ ያመላከታቸው ነጥቦች እንዳሉም ያስረዳሉ። በዚህም\nከአደረጃጀት ፣ ከፋይናንስ፣ ከሰው ኃይልና ሌሎችም ጉዳዮች አንፃር ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚቻል ተስፋ የተጣለበት መሆኑን\nይጠቅሳሉ፡፡ በሪፎርሙ ላይ የሴክተሩ ችግሮች የተለዩ ሲሆን በተመሳሳይ መፍትሄዎች መመላከታቸውንም ያክላሉ። ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ\nተግባራዊ የሚደረገውና ከስፖርት ሪፎርሙ የሚቀዳው የ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ ዘርፍን የተሻለ እንደሚያደርገውም ያላቸውን እምነት\nይገልፃሉ፡፡ አቶ እንድሪስ በበኩላቸው፤\nበቀጣይ ዓመት ተግባራዊ የሚደረገው ስትራቴጂክ ዕቅድ ትኩረት ያደረጋቸው አንኳር ጉዳዮች መኖራቸውን በመጥቀስ በሴክተሩ በቀጣይ\n10 ዓመታት በትኩረት የሚሰራባቸው ተብለው የቀረቡት ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች እንዳሉ ይናገራሉ:: በመጀመሪያ መንግሥታዊ የስፖርት\nአደረጃጀቶችን የመፈፀም እና የማስፈፀም አቅም በማጎልበት፤ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን እና የአሠራር ሥርዓቶችን ተግባር ላይ ማዋል\n፤ ሕዝባዊ የስፖርት አደረጃጀቶችን በዓለም አቀፍ እና በአገር አቀፍ መስፈርቶች መሠረት ማደራጀት የስትራቴጂክ እቅዱ ትኩረት መሆናቸውን\nያስቀምጣሉ:: በሁለተኛ ደረጃ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የማሰልጠኛ ማዕከላት ተደራሽነት፣ ሕጋዊነት እና ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን\nመሠረት በማድረግ በጥራት የሚገነቡበትን ስልት ሥራ ላይ ማዋል ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን ያስረዳሉ። በአህጉር እና ዓለም አቀፍ የውድድር\nመድረኮች በተፈጥሮ ብቃታቸውን መሠረት በማድረግ አገራችንን የሚወክሉ እና ውጤታማ የሆኑ ተተኪ ስፖርተኞችን በሳይንሳዊ ስልጠናዎች\nማፍራት ትኩረት ተደርጎ የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑንም ያብራራሉ፡፡ ስፖርት ለማህበራዊ ልማትና ለአገር ብልፅግና ፣ ለሕዝቦች መቀራረብ\n፣ ለገፅታ ግንባታ እና ለቱሪዝም ዕድገት መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ትኩረት ሰጥቶ መስራትም የስትራቴጂክ እቅዱ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው።\nበስትራቴጂክ ዕቅዱ የተጠቀሱትን አንኳር ጉዳዮች መሠረት አድርጎ የተዘጋጀው ግብ ወደ ተግባር መቀየር ከተቻለም የስፖርት ሴክተሩ\nውጤታማ መሆን እንደሚችል እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡የባህልና ቱሪዝም\nሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀብታሙ ሲሳይ፤ በአገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲ ባለፉት ሁለት አስር ዓመታት የተመዘገቡ በርካታ አበረታች\nውጤቶች ቢኖሩም የአገራችን የስፖርት ዕድገት ከዕድሜው አኳያ ሲመዘን በሚፈለገው ደረጃ ባለማደጉ ብዙ መስራት እንደሚጠበቅ ያመላክታሉ።\nበአሁኑ ወቅት መንግሥት ስፖርቱን እንደ አንድ የልማትና ብልፅግና መሣሪያ አድርጎ በመውሰድ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየሰራ እንደሚገኝ\nየሚናገሩት አቶ ሃብታሙ ፤ የስፖርት ዘርፍ በታሪኩ በዚህ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት እንደማያውቅ ያብራራሉ:: የብሔራዊ የስፖርት ምክር\nቤት በኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ሰብሳቢነትና የበላይ ጠባቂነት መመራቱ መንግሥት ለስፖርቱ ሴክተር የሰጠውን\nትኩረት እንደሚያሳይም ያስቀምጣሉ፡፡ በመሆኑም የስፖርት ዘርፍን ከትናንት በተሻለ መልኩ ዛሬ ትኩረት በማግኘቱ ዕድሉን በአግባቡ\nበመጠቀም ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን አርብ ጥር 22/2012ዳንኤል ዘነበ\n", "passage_id": "03113203decaadfcc71b27a06362f673" }, { "passage": "አሁን ስፖርት ሁሉንም ነገር እየሆነ መጥቷል»። ይህንን አባባል በድፍረት ለመናገር ያስገደደን በዓለማችን ላይ ያለውን ተወዳጅነት እና የተደራሽነት ስፋት ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው። ስፖርት በተለይ ደግሞ እግር ኳስ እና የኦሎምፒክ ውድድሮች በምድራችን ላይ ቀዳሚ ተወዳጅነትን እያተረፉ መጥተዋል ብለን ብናወራም ማጋነን አይሆንብንም። የእረፍት ቀናት\nበስፖርታዊ ጨዋታዎች ይደምቃሉ።\nበመኖሪያ በቤቶች፣ መዝናኛ\nስፍራዎች ስፖርታዊ ትዕይንቶች\nበቴሌቪዝን መስኮቶች ይኮሟኮሟል። ሳቅ፣ ግርምት፣\nብስጭትን ጨምሮ በርካታ\nትዕይንቶች በስፖርት ስፍራዎች\nበየደቂቃው እና ሰከንዱ\nይከሰታሉ። የዚህ ስሜት\nምንጭ እና ተዋኒያን\nደግሞ በማዘውተሪያ ስፍራዎቹ\nየሚፋለሙት ስፖርተኞች ናቸው።\nበዚህ መድረክ ላይ\nመሳተፍ የሚያስገኘው ጥቅም\nደግሞ የትዬለሌ ነው።\nረብጣ ገንዘብ እና\nዝና ከጥቅሞቹ መካከል\nናቸው። ይሄ ደግሞ\nፉክክሩን የበለጠ ያንረዋል።\nበእግር ኳስ\nሜዳ፣ በመሮጫ ትራኮች\nላይ እልህ አስጨራሽ\nስሜት ፈታኝ ፉክክሮች\nይካሄዳሉ። ኧረ እንደውም\nከዚያም ከፍ ይላል።\nከመጫወቻ ሜዳ ውጪ\nቅድመ ግብግቦችም አይጠፉም።\nየስነ ልቦና ጦርነቱ\nየአናብስቱን ድርሻ ይወስዳል።\nምክንያቱም ማሸነፍ ብዙ\nትርጉም አለው። በዛሬው\nየእሁድ ገፃችን ከስፖርቱ\nዓለም አሸንፎ የመውጣት\nሽኩቻ ውስጥ አንዱን\nመዘዝ አድርገን በዝርዝር\nእየተመለከትን በመግቢያችን ላይ\n«አሁን ስፖርት ሁሉንም\nነገር እየሆነ መጥቷል»\nያልንበትን ምክንያት ለማስረዳት\nእንሞክር። የወሲብ ትንኮሳ\nእንደ ስኬት መንገድ\nበስፖርቱ ዓለም ስኬታማ ሆኖ የመውጣት ፍላጎት በሁሉም ስፖርተኞች ዘንድ በጥብቅ የሚፈለግ ጉዳይ ነው። ይህ ከፍ ያለ ፍላጎት ደግሞ ሽኩቻ እና ብዙ አሻጥር ይበዛበታል። ከዚህ ውስጥ አሰልጣኞች፣ የስፖርት ማኔጀሮች እንዲሁም  በዙሪያው ያሉ አካላት ወዳልተፈለገ ድርድር እና ግዴታ ውስጥ የሚያስገቡ ድርጊቶች ይጠቀሳሉ። ከነዚህ ውስጥ ደግሞ የወሲብ ትንኮሳ እና ጥቃት አንዱ ነው። አሁን ላይ ይህ\n«የወሲብ መሞዳሞድ»\nበከፍተኛ ደረጃ እጅግ\nበረቀቀ መንገድ እየተፈፀመ\nእንደሆነ በጉዳዩ ላይ\nጥልቅ ጥናት የሚያደርጉ\nባለሙያዎች ይናገራሉ። እራስን\nከፍ ያለ ዝና\nላይ ለማስቀመጥ ፣\nበመታለል አሊያም ደግሞ\nበሚደርስባቸው ዛቻ እና\nማስፈራሪያ ሴት ስፖርተኞች\nበብዛት የጥቃቱ ሰለባ\nይሆናሉ። እራሳቸውን መስዋዕት\nአድርገው የውስጥ ፍላጎታቸውን ያሳካሉ። ወይም\nደግሞ በሚወዳደሩበት የስፖርት\nአይነት ምንም እንኳን\nብቃት ቢኖራቸውም የሚጠይቁትን ማሟላት ስላልቻሉ\nብቻ ከመንገዳቸው የሚሰናከሉ\nበገፍ ይኖራሉ። ዓለም አቀፉ የኦሎምፒክ\nኮሚቴ ይህ ጉዳይ\nእጅግ አሳሳቢ መሆኑን\nተረድቶ ሰፊ ውይይት\nእና ጥናት በባለሙያዎች ካደረገ በኋላ\nአንድ መደምደሚያ ላይ\nደርሷል። በሁሉም የስፖርት\nአይነት እና ደረጃ\nበተለይ በሴቶች ላይ\nየሚደርስ የወሲብ ጉንተላ\nእና መደራደር መኖሩን\nአረጋግጧል። በአትሌቲክስ እና\nአንዳንድ እውቅ ስፖርቶች\nላይ ደግሞ ጉዳዩ\nጎልቶ ይወጣል። የመጀመሪያው ተንኳሾቹ ስልጣን\nእና ኃላፊነት ላይ\nያሉት ሲሆኑ በቀጣይነት\nየሚቀመጡት ደግሞ በስፖርቱ\nላይ አብረው ተሳታፊ\nየሆኑት ናቸው። የኦሎምፒክ ኮሚቴው አገኘሁት\nባለው መረጃ ጥቃት\nእና ጫና የሚደርስባቸው አትሌቶች የአካል\nእና የስነ ልቦና\nጫና ይደርስባቸዋል። ሆኖም\nስኬታማ ለመሆን ስለሚፈልጉ\nብቻ ጉዳዩን አፍነው\nእንደሚይዙት አረጋግጧል። በተለይ\nከዚህ ጫና ጋር\nተያይዞ የተመኙትን ስኬት\nሳያጣጥሙ ለከፍተኛ ድብርት፣\nጭንቀት እና የአእምሮ\nበሽታዎች ተጋላጭ ይሆናሉ።\nየአትሌቲክስ ማህበሩ ፖሊሲ\nበተለያዩ ስፖርቶች ላይ\nየወሲብ ትንኮሳ በስፋት\nመኖሩን ጥናቶች አመልክተዋል። ሆኖም ግን\nይህን ጉዳይ ለመከላከል\nከፍተኛ ጥረት በማድረግ\nላይ ያለው የስፖርት\nተቋም ዓለም አቀፉ\nየአትሌቲክስ ማህበሮች ፌዴሬሽን\n«አይ ደብል ኤ\nኤፍ» ነው። በቅርቡ\nአንድ መረጃ ይፋ\nበማድረግም በጉዳዩ ላይ\nጥብቅ እርምጃ ለመውሰድ\nእንደተዘጋጀ ይፋ አድርጓል።\nአይ ደብል ኤ\nኤፍ በስፖርቱ ዓለም\nላይ እየደረሰ ያለው\nወሲባዊ ጥቃት እና\nትንኮሳ አትሌቶቹ ላይ\nከፍተኛ የስነ ልቦና\nጫና እያደረሰ መሆኑን\nይፋ አድርጓል። ከሳምንታት\nበፊት የካውንስል ስብሰባ\nበቦነስ አይረስ ከተማ\nባደረገበት ወቅትም በዚህ\nዙሪያ ምን አይነት\nአቋም እንዳለው ለመላው\nየስፖርት ቤተሰብ አሳውቋል።\nበመግለጫው ላይ ይፋ\nያደረጋቸው ነጥቦች ለሁሉም\nአባል አገራት ፌዴሬሽኖች\nስፖንሰር አድራጊዎች እና\nለራሱ ለፌዴሬሽኑ መመሪያ\nሆኖ እንደሚያገለግልም ነው\nየታወቀው። ወሲባዊ ትንኮሳን\nለመከላከል እና ስፖርቱን\nከተጋረጠበት አደጋ ለመጠበቅ\nጥብቅ ህጎችንም አውጥቷል።\nተወዳዳሪዎች እና አሰልጣኞች፣ የስፖርት አመራሮች\nሊያከብሯቸው የሚገቡ ህጎችንም\nይፋ አድርጓል። ይህ\nጉዳይ ማህበሩን ምን\nያክል ፈተና ውስጥ\nእየከተተው እንደመጣ ያመላከተ\nነበር። አይ ደብል ኤ\nኤፍ በርካታ ውድድሮችን\nበማዘጋጀት እና በስሩ\nበመምራት ይታወቃል። እነዚህ\nውድድሮቹ በዓለም ላይ\nተወዳጅነታቸው ከፍተኛ ነው።\nሆኖም ግን ባልተፈቀዱ\nአበረታች መድሃኒቶች፣ የሙስና\nቅሌቶች እና በዋናው\nርዕሳችን ያነሳነው «የወሲብ\nትንኮሳዎች እና ቅሌቶች»\nይታመሳል። እነዚህን ፈተናዎች\nለማለፍም በርካታ ህጎችን\nእና ፖሊሲዎችን በማውጣት\nለመከላከል ሙከራ እያደረገ\nይገኛል። ፊላንድ ቴምፐር ከ20\nዓመት በታች የዓለም\nወጣቶች ሻምፒዮናን አስተናግዳለች። በዚህ ወድድር\nላይ የአይ ደብል\nኤ ኤፍ ባለሙያዎች\n500 ወጣት አትሌቶችን በመምረጥ\nጥናት አድርጓል። ጥናቱ\nትኩረት ያደረገውም በወሲብ\nትንኮሳ እና ዳር\nዳርታ ላይ ስፖርቱ\nምን ያህል ችግር\nውስጥ እንደገባ ለይቶ\nለማወቅ እንዲሁም ህግ\nለማውጣት ነበር። በወቅቱ ጥናቱን በመስራት\nየተሳተፉት የአይ ደብል\nኤ ኤፍ የጤና\nባለሙያ ዶክተር ፓኦሎ\nኢሚሊዮ አዳሚን ጉዳዩ\nበስፖርቱ ማህበረሰብ ላይ\nበተለይም ደግሞ በአትሌቲክሱ ላይ ምን\nያህል አሳሳቢ እየሆነ\nእንደመጣ ለመለየት ጥረት\nአድርገናል ብለዋል። «ይሄ\nጉዳይ በስፖርቱ ላይ\nአይኖርም የሚል ድምዳሜ\nላይ መድረስ በጣም\nሞኝነት ነው። ምክንያቱም\nየአንድ ግለሰብ ባህሪ\nበሁሉም ቦታ ተመሳሳይ\nነው» በማለት በአትሌቲክሱ ላይ ችግሩ\nጥላውን እንዳጠላ ይናገራሉ።\n«ጥናቱን\nለማድረግ በልምምድ ሜዳ\nላይ በተገኘንበት ጊዜ\nተሳታፊዎቹ በወረቀት ላይ\nያሰፈርናቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ\nሙሉ ፍቃደኝነታቸውን ከጥሩ\nፈገግታ ጋር ለግሰውናል። ይሄ ጉዳዩ\nምን ያክል አሳሳቢ\nእንደነበር ያመላከተን ነው»\nበማለት ዶክተር ፓኦሎ\nትዝብታቸውን ገልፀዋል። የጥናቱን\nውጤት በዓመቱ መጨረሻ\nላይ ማህበሩ በሚያደርገው ስብሰባ ይፋ\nእንደሚያደርግ አስታውቀዋል። የሚገኘው\nውጤትም ለሚወጡ ህጎች\nእና መመሪያዎች ግብአት\nሆኖ ያገለግላል ብለዋል።\nዓለም አቀፉ ነፃ\nየአትሌቶች ማህበር «ኤ\nዩ አይ» በበኩሉ\nማንኛውም አትሌት ለሚደርስበት ፆታዊ ተኮር\nትንኮሳ ለሚያቀርበው ምላሽ\nለመስጠት ነፃ የቅሬታ\nማቅረቢያ (www.athleticsinteg­rity.org) ድህረ ገፅ ይፋ\nካደረገ ቆየት ብሏል።\nዶክተር ፓኦሎ በዚህ ጉዳይ ላይ በርካታ ጥናቶችን ለማድረግ እና ስፖርቱ ነፃ የውድድር ሜዳ እንዲሆን ለማስቻል እቅድ መንደፉን ይናገራሉ። ሁሉም አትሌቶች ከዚህ መሰል ጫና መላቀቅ ይኖርባቸዋል የሚል ጠንካራ አቋም መኖሩን ያመላክታሉ። በዚህ ችግር የስነልቦና እና አካላዊ ጥቃት የሚደርስባቸውን አትሌቶች ጫና ለመከላከልም አይ ደብል ኤ ኤፍ ቁርጠኛ መሆኑን ነው የሚያስረዱት። «ይሄ ጉዳይ ከስፖርቱ መራቅ አለበት። ሁሉም አትሌቶች ይህን መሰል አጋጣሚ ውስጥ ራሳቸውን ካገኙ እንዴት መከላከል እንዳለባቸው እናስተምራቸዋለን» ነው ያሉት።አዲስ ዘመን መጋቢት 29 /2011 ", "passage_id": "c9ba8dc973d8a0e9bf06789386d5eb1c" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ በአትሌቲክሱ ዘርፍ ያላትን ስምና ዝና እንዲሁም ውጤት ለማስቀጠል ሲባል በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት የተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ውድድሮችን ለማድረግ ቅድመ ማጣሪያ ውድድሮችን ማድረግ የተለመደ ተግባር ሆኖ ቆይቷል፡፡ በየዓመቱ ከሚደረጉ ቅድመ ማጣሪያ ውድድሮች አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ይጠቀሳል፡፡ በኦሮሚያ ክልል አሰላ ከተማ ላይ ተተኪ አትሌቶችን ለማግኘት ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በታች አትሌቶች ክለቦቻቸውን በመወከል ያላቸውን አቅም ማሳየት ከጀመሩ ሰባተኛ ዓመታቸውን ይዘዋል፡፡ ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ የሚካሄደው ሻምፒዮናው በትናንትናው እለት በአሰላ አረንጓዴው ስታዲየም በይፋ ተጀምሯል።የውድድሩ ውጤታማ አትሌቶች የውድድሩ ዓላማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲካሄዱ የወጣቶች ውድድር አገራቸውን ወክለው የሚካፈሉ እንደሆነ የተጠቀሰ ሲሆን ፤ቀጣይ ለአገሪቱ አትሌቲክስ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እንደሆነም ጭምር መሆኑን ተነግሯል። የሻምፒዮናው አላማ ይሄንን መልክ የያዘ ቢሆንም ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ከውድድሩ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማግኘት ያለመ ቢሆንም ፤የዕድሜ ተገቢነት ችግር አሁንም ሊፈታ ያልቻለ ጉዳይ እንደሆነ የተለያዩ ባለሙያዎች እየተናገሩ ይገኛሉ።ፌዴሬሽኑም ይህን መቆጣጠር አስቸጋሪ እንደሆነበትና ክልሎችና ክለቦች ሲጠየቁ ክለብ ሲገባ ዕድሜውን እንዲቀንስ ተደርጎ የተመዘገበበትን ሀሰተኛ የሆነ ማስረጃ እንደሚያቀርቡ በተደጋጋሚ ሲነገር ነበር። በዚህ ምክንያት ዕድሜያቸውን ለመቆጣጠር አስቸጋሪ መሆኑ ይነሳል። ከዚህ በመነሳትም የዘንድሮው የሰባተኛው ከ20 ዓመት በታች የታዳጊዎች ሻምፒዮና ከዚህ ችግር የጸዳ በሆነ መልኩ ተጀምሮ የሚጠናቀቅ ስለመሆኑ ጥያቄን አስነስቷል። ሻምፒዮናው ከትናንት ማለዳ ጀምሮ መካሄድ ጀምሯል።በእለቱ ከተካሄዱ ውድድሮች የስሉስ ዝላይ ሴቶች ከኦሮሚያ ክልል እንደቴ ሮቤ 11.67 ሜትር በመወርወር አንደኛ ስትሆን ፣ ኡጁሉ ኦዶላ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 11.64 በመወርወር ሁለተኛ ፣ ኩለኒ ድሪባ ከኦሮሚያ ክልል 14.54 በመወርወር ሶስተኛ ሆነዋል። ዲስከስ ውርወራ ወንዶች የሲዳማ ቡና ለማ ከተማ 47.44 በመወርወር አንደኛ ሲሆን፣ የመከላከያው ጌታቸው ተመስገን እና የአማራ ክልሉ አየነው ኮሴ 47.23 እና 42.80 በመወርወር ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል። በሴቶች ዲስከስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ መሪያምመዊት ፀሀዬ 38 .73 ሜትር በመወርወር አንደኛ ሆናለች። ማርታ በቀለ ከጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ 34.99 ሜትር በመወርወር ሁለተኛ ፣ ትንጓደድ ተሰማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከንግድ ባንክ 32.89 በመወርወር ሶስተኛ ሆናለች። የወንዶች 10 ሺ ሜትር ሌላው በትናንትናው እለት የተካሄደ ውድደር ሲሆን ጸጋዬ ኪዳኑ 29፡34፡27 ሰዓት በመግባት ከመስፍን ኢንጂነሪንግ አሸናፊ ሲሆን እርሱን ተከትሎ ሚልኬሳ መንገሻ ከሰበታ ከነማ ክለብ 29 ፡35፡65 ሁለተኛ እንዲሁም ወርቅነህ ታደሰ ከኦሮሚያ ክልል 29፡39፡98 ሰዓት አስመዝግቧል።በአሰላ አረንጓዴ ስታዲየም የሚካሄደው ሻምፒዮናው ለቀጣይ አራት ቀናት በድምቀት የሚቀጥል መሆኑን ታውቋል። ከጥር 15 እስከ 19 ቀን 2011 ዓ.ም በሚካሄደው ውድድሩ 9 ክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም 34 የተለያዩ_ ክለቦችና ተቋማት ተካፋይ ሆነዋል።አዲስ ዘመን ጥር 16/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "c90b10f6d6ef9e95a9b4a3ed0f3565c4" }, { "passage": " ከዓለም እስከ አህጉር፣ ከአህጉር እስከ አገር፣ ከአገር እስከ መንደር ከዚያም ማህበረሰብ እስከ ግለሰብ፣ በስፖርት ልቡ ያልተሳበና በፍቅሩ ያልተንበረከከ የለም።ስፖርት ሰላም ፣ፍቅር ፣የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም።ሁለት የተለያዩ አገራት ያወዳጃል። በአገር ፍቅር ስሜት ያስተሳስራል።ያፋቅራል።በእርግጥ አንዳንዶች ውጤትን ከስፖርታዊ ጨዋነት አስበልጠው የግል ጥቅማቸውን ሲያስቀድሙ ይስተዋላል። ከዚህ በአንፃሩ የግል ፍላጎታቸውን ችላ በማለት በስፖርታዊ ስነ ምግባር የታነፁ መኖራቸው የማይካድ ሃቅ ነው።በአትሌቲክሱ የውድድር ፍልሚያ ኬንያውያን በተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ውድድሮች ላይ በርካታ ወገኖችን አስደንቀዋል።አስጭብጭበዋል።በውድድር አሸናፊ ሆነው የታዩትን ያህልም ከአንዴም ሁለት ጊዜ በስፖርታዊ ጨዋነትና ሰብዓዊነት ተግባር የታነፁ ስለመሆናቸውም አስመስክረው የሚሊየኖችን ልብ ሲያሸንፉ ታይተዋል።።የምስራቅ አፍሪካዊቷ አገር አትሌት ከሰሞኑም ይህን በስፖርታዊ ጨዋነት መርህ የታነፀ ሰብዓዊነት ተግባር ደግሞ አሳይቷል።ትዕይንቱ የተከሰተው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማህበር የነሃስ ሜዳሊያ በሚሰጠውና ከቀናት በፊት በተካሄደው የናይይጄሪያ ዓለም አቀፍ የ10 ኪሎ\nሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ነው።የታሪኩ ባለቤት ሲሞን ቺፕሮት ይባላል።ኬንያዊ የረጅም ሩጫ አትሌት ነው።በዚህ የ10 ኪሎ\nሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ሲሳተፍ አራተኛው ሲሆን፣ ከሶስት ዓመት በፊት ደግሞ ባለድል መሆን ችሏል።ባሳለፍነው አመት ደግሞ ሁለተኛ ሆኖ ጨርሷል።ክስተቱ እንዲህ ነው። ሲሞን ቼፐሮት የዘንድሮውን ውድድር እየመራ ለመጨረስ የተወሰኑ ሜትሮች ብቻ ቀርተውታል።ውድድሩን ለሁለተኛ ጊዜ በማሸነፍ የመጀመሪያው የሚሆንበትን ታሪክ ለመፃፍ ማንም ሊያቆመው አይቻለውም።ይሁንና በዚህ ቅፅበት ሌላኛው የአገሩ ልጅና ብርቱ ተቀናቃኙ የሆነው ኬኔት ኪፕኬሞይ ድንገት ሲዝለፈለፍ ይመለከታል።ክስተቱን ያስተዋለው ሲሞን ቼፕሮት ግን የአገሩን ልጅ ጥሎት ለመግባት አልወሰነም።ውድድሩን አሸንፎ አንደኛ የመባል ስሜቱን አላዳመጠም።ውድድሩን ለሁለተኛ ጊዜ በማሸነፍ የመጀመሪያው የሚሆንበት ታሪክ ለመጻፍ አልቸኮለም።አትሌቱ የተፎካካሪውን ውድቀት እንደ መልካም አጋጣሚ ከመጠቀም ይልቅ ብዙዎቹን ባስገረመ መልኩ ሩጫውን በማቋረጥ ጓደኛውን ከወደቀበት ደግፎ አንስቶ ልባዊ ወንድምነቱን በማሳየት በርካታ ወገኖችን አስደምሟል። ሁለቱ አትሌቶችም ቀስ ብለው በመሮጥ ውድድሩን 15ኛ እና\n16ኛ ሆነው የፈፀሙ ሲሆን አንደኛ መውጣት የሚችለው ሲሞንም ተሸንፏል።አትሌቱ ከፊቱ የሚጠብቀውን የወርቅ ሜዳሊያና የአሸናፊነቱን ሽልማት ገንዘቡን በመተውና ይህ ሁሉ ከሰው እንደሚያንስ በማሳብ የፈፀመው መልካም ተግባር በሚሊየን የሚቆጠሩ ልቦችን ማሸናፍ ችሏል።የወርቅ ሜዳሊያውን ትቶ ከወርቅ በላይ የሆነ ጀብዱ በመፈፀም፤ ከወርቅ ሜዳሊያው ይልቅ ሰብአዊነት እንደሚልቅ ለመላው ለዓለም   አሳይቷል።ሜዳሊያ ሳይሆን ልብ ያሸነፈውና በውድድሩ ስፍራ ሆነው ውድድሩን የተመለከቱትን በሺዎች የሚቆጠሩ ብቻም ሳይሆን በአህጉር ዓቀፍ ደረጃ በቴሌቪዥን መስኮት የሚመለከቱትን ያስደነቀ አትሌት ፤ማሸነፍ ማለት ሁሌ አንደኛ መውጣት ማለት አይደለም፤ሁሌ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኛት አይደለም። አንዳንዴ ተሸንፈህ አሸናፊ ትሆናለህ፣ መጨረሻ ወጥተህ ክብርን ጀግንነትን ትጎናፀፋለህ አሰኝቷል።‹‹በአንድ ወቅት አባቴ፤ በመንገድህ ላይ የታመመ ሰው ስትመለከት አልፈኸው ጉዞህን አትቀጥል፤ ይልቅ እርዳው፤ ብሎኝ ነበር፤ የአገሬውን ልጅ ወድቆ ስመለከተው ይህ ወደ አእምሮዬ መጣ፤ እናም ለራሴ ሳላስብ ልረዳው ወሰንኩ ››ያለው አትሌቱ፤ መሰል ተግባሩም ለመጪው ትውልድ አርእያነት ያለው ስለመሆኑ ተናግሯል።የአትሌቱ ተግባርም የወርቅ ሜዳሊያ ከማግኘት ይልቅ ወርቃማ ልብ መያዝ ይበልጥ ያነግሳልና ይህም እውነተኛው የስፖርት ጽንሰ ሃሳብ መገለጫ ነው አሰኝቷል። በዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር የናይጄሪያ ተወካይ ማይክ ልቴሟግቦር አትሌቱን ‹፣ጀግናችን››ሲሉ አሞካሽተውታል፡፡ለፈፀመው የሰብዓዊነት አኩሪ ገድልም አንድ ሚሊየን ሽልንግ አበርክተውለታል።የቺፕሮትን ተግባር\nበማወደስ፤ ተረጂው አትሌት\nበበኩሉ፤ ‹‹ሁሉም አትሌት\nይህን መሰል ተግባር\nአይፈፅምም፤ሲሞን መልካም\nሰው ነው፤ በውድድሩ\nእኔን ለማርዳት ያሰው\nመልካምነትም እጅጉን አስድንቆኛል››\nሲል ተደምጧል። አሸንፎ\nሜዳሊያውን ከወሰደው ኢትዮጵያዊ\nበላይ ሲሞን ጀግና\nተብሎ ዘላለማዊ ስምና\nዝናን አትርፏል።አዲስ ዘመን ግንቦት 27/2011 ", "passage_id": "ea9ee4c32daedd909149824d13b5ab5d" }, { "passage": "በ1990 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የስፖርት ፖሊሲ ፣ክለቦች ደረጃ በደረጃ በሂደት ህዝባዊ አደረጃጀት እንዲኖራቸው ማድረጉን ያስገነዝባል፡፡ ስፖርቱ ከመንግሥት በጀትና ድጎማ ደረጃ በደረጃ የሚላቀቅበትንና ራሱን የሚችልበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠርም የፖሊሲው የትኩረት አቅጣጫ ነው። ይሁንና ፖሊሲው ከወጣ ሁለት አስርት ዓመታትን ቢያስቆጥርም እንደተቀመጠው አቅጣጫ እና ፍላጎት የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ በግልፅ ይታያል። በአሁኑ ወቅት ጥቂት ከሚባሉት በስተቀር አብዛኞቹ የአገሪቱ ክለቦች በመንግሥት ጉያ ስር የተደበቁና ህዝባዊ አደረጃጀት የሌላቸው ናቸው። ከአገሪቱ ክለቦች 90 በመቶ የሚሆኑት የሚተዳደሩት በመንግሥት ድጎማና በልማት ድርጅቶች ወጪ ነው። ህልውናቸው መሰረቱን ያደረገው በመንግሥት ወጪ እንደመሆኑም ድጎማ ሲቀር የክለቦቹ አደረጃጀትም አብሮ ይቀራል። መዋቅር ሲስተካከልና ሲለዋወጥ ክለቦቹም አብረው ይለወጣሉ። አሊያም ይፈርሳሉ። የልማት ድርጅቶቹ ህልውናቸው አደጋ ውስጥ ሲወደቅ ወይም ወደ ሌላ ሲዛወሩ የክለቦቹም ህልውና ይታመማል፤ያበቃል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦች በተለይም የፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ክለቦች ራሳቸውን ችለው ባልተደራጁበት በአሁኑ ወቅት በጣም ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ ወጪ ሲደረግ ይስተዋላል። ይህም የክለቦች ወጪና ገቢ እንዳይመጣጠን እያረገ ነው። የወጪ ዕድገት ጣራው ቀና ብለን መጨረሻውን ለማየት አስችጋሪ ሆኗል። ክለቦች በዚህ መልኩ ያለቅጥ የሚያሽከረከሩት ገንዘብ ከየት ተገኘ፣ከፋዩስ ማነው?» ተብሎ ሲጠየቅ ከመንግሥትና ከህዝብ በጀት የሚለው መልስ ፈጥኖ ይመጣል። ይህን ወቅታዊ ውጤትን ፍለጋ ብቻ «ነገ ለራሱ ይወቅበት» በሚል ከመንግሥት ካዝና ተዝቆ የሚሰጥ የክለቦች ቅጥ ያጣ የገንዘብ አወጣጥን የተመለከቱ የዘርፉ ባለሙያዎችም፤ድርጊቱ ማሰሪያ ካልተበጀለት የኋላ ኋላ የከፋ አደጋ እንደሚያስከትል እየጠቆሙ ናቸው፤በዚህ ዓይነቱ ድርጊት የተነሳም ክለቦችም ሆኑ የአገሪቱ እግር ኳስ ህልውና አደጋ ላይ ስለመሆኑ እያሳሰቡ ይገኛሉ። ይህን ሃሳብ ከሚጋሩት የዘርፉ ባለሙያዎች መካከል ረዳት ፐሮፌሰር ወንድሙ ታደሰ ዋነኛው ናቸው። ረዳት ፐሮፌሰር ወንድሙ በ1990 ዓም የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ የስፖርት ፖሊሲን ካረቀቁት አንዱ ሲሆኑ፣ በአሁኑ ወቅትም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ትምህርት ክፍል በምርምርና መምህርነት እያገለገሉ ናቸው። አዲስ ዘመን ጋዜጣም በክለቦች ወቅታዊ ወጪ ላይ ከባለሙያዎች የሚነሱ ስጋቶችን ዋቢ በማድረግ ከረዳት ፕሮፌሰር ወንድሙ ታደሰ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው አዘጋጅቶታል።አዲስ ዘመን፡- የፖሊሲው አቅጣጫና የክለቦቻችን አደረጃጀት ምን ያህል ተጣጥሟል? ረዳት ፐሮፌሰር ወንድሙ!- ክለቦች በውድድር መድረኮች ለሚኖራቸው ውጤታማነትና ቆይታ በተለይም ለህልውናቸው ቀጣይነት የሚከተሉት የክለብ አደረጃጀት እጅግ ወሳኙን ድርሻ ይኖረዋል። አደረጃጀቱ ህዝባዊ መሰረተን የተከተለ እንዲሆን ማድረግ ደግሞ ትክክለኛ አማራጭና ለውጤታማነታቸው ዋነኛ ቁልፍ ነው። የአገሪቱ የስፖርት ፖሊሲ ክለቦች ደረጃ በደረጃ ወደ ህዝባዊ አደረጃጀት እየተለወጡ በስፖርቱ ልማት ላይ መሳተፍ እንዳለባቸው ያመለክታል። ይህ ግን እየሆነ አይደለም። ስለ ክለብ አደረጃጀትና አወቃቀር ጠንቀቆ የሚያውቅ ሰው እንዲሁም ክለቦች እንዴት መደራጀት እንዳለባቸው በጥናት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ የ23 ዓመታትን ያስቆጠረ ሰነድ ሀገሪቱ ቢኖራትም ፣በዚህ መንገድ ተጓዙ የሚል መሪ ግን አልተገኘም። ይህን የሚከታተል ፖሊሲውን የሚያስፈፅም የለም። መንገዱ ጠፍቶናል። እናም በጭለማ እየተጓዝን ፊደል ያልቆጠረ ሰው የሚሠራውን እየሠራን ነው። አዲስ ዘመን፡- የፖሊሲው አቅጣጫና የክለቦቻችን አካሄድ መግባባት እንደተሳናቸው የሚያሳዩ ማስረጃዎች ምን ይሆኑ?ረዳት ፕሮፌሰር ወንድሙ፡- በአሁኑ ወቅት ስፖርት ከመዝናኛነቱ ባለፈ ሥራ / ቢዝነስ/ ነው። ማንኛውም ክለብ ባለቤት ያስፈልገዋል። የክለብ ባለቤት ገቢ ያመነጫል። በገቢው ተጫዋች ይገዛል፤ይለውጣል፤ትርፍ ያገኛል። የክለቦች አደረጃጀት ህዝባዊ መሰረትን የተከተለ ከሆነ ደግሞ ይህን በቀላሉ ማሳካት ይቻላል። ይሁንና በአሁኑ ወቅት ራሱን የቻለ ህዝባዊ አደረጃጃት ያለው ክለብ የለም። ክለቦቻችን የራሳቸውን ገቢ አመንጨተው የሚተዳደሩ አይደሉም። መሰል አሠራሮችን የሚተገብሩም አይደሉም። አብዛኞቹ የመንግሥትን ገንዘብ የሚበሉ ጥገኛና ካዝና ተቋዳሽ ናቸው። ትልቅ የገቢ ማመንጫ መዝናኛና ሜዳ ያለው ክለብ የለም ከጋራ ስታዲየም ከሚገኝ ገቢ የሚጠቀም እንጂ የራሱ ስታዲየም ገቢ ያለው ክለብም አይታይም። ሌላው ዓለም ይህን የጀመረው በሃያኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ነው። ዛሬ ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ላይ ነን። እኛ ግን በጣም ገና ነን። ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ የበላይ ተቋም / ፊፋ/ እያዘነልን እንጂ አሁን የክለቦቻቸውን ቁመና ከመስፈርት በታች ነው። አዲስ ዘመን፡- ክለቦች ራሳቸውን ችለው ባልተደራጁበት በአሁኑ ወቅት በጣም ክፍተኛ ገንዘብ ወጪ በማድረግ በተለይ የውጭ ተጫዋቾችን ማስፈረማቸውን እንዴት ይገልፁታል? ረዳት ፕሮፌሰር ወንድሙ፡- ምንም እንኳን አብዛኞቹ ክለቦች ራሳችውን ችለው መቆምና ገቢ መፍጠር ባይሆንላቸውም ከፍተኛ የሆነ ገንዝብ ወጪ በማድረግ ላይ ተጠምደዋል። ይህ ገንዘብ ደግሞ የመንግሥትና የህዝብ ሀብት ነው። ገንዘቡም በተለይም ታዳጊዎች ላይ በመሥራት ምርጦችን ከማፍራት ይልቅ ከውጭ ተጫዋቾችን በማምጣት ሲውል ይስተዋላል። ይሁንና በቀዳሚነት ተጫዋቾችን ከውጭ መግዛት ለምን አስፈለገ? ክለቦቻችን ፕሮፌሽናል አይደሉም። ፕሮፌሽናል ክለቦች ከገዙት ተጫዋች ቢሊየን ዶላሮችን ያገኙበታል። እኛ የውጭ ተጫዋቾችን አምጥተን ምን አገኘን? በአሁኑ ወቅት ወርሃዊ የአንድ ተጫዋች ክፍያ ሦስት መቶ ሺ ብር ደርሷል ከተባለ ከየት መጥቶ ነው የሚከፈለው። ክለቡ የሚያመነጨው ሀብት ካለና አትርፎ ከሆነ በጣም ጥሩ ነው። ይሁንና ምንም ትርፍ የሚያመጣ የለም። ምንም ተጨባጭ ትርፍ በሌለው ገና ለገና ከማን አንሼ በሚል ለአንድ ተጫዋች ሦስት መቶ ሺ መክፈል አግባብ አይደለም። ይህ ዓይነት መካሄድም በዓለም አቀፍ ደረጃ በጣም ያስተቻል። በአጠቃላይ በጭፍን እየተጓዝን ነው። ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለውም። ስፖርቱን የሚገድል እንጂ የሚያሳደግ አይደለም። ይህን ዓይነት ተግባር የዕድገት ደረጃ ማሳያ አይደለም። እኔ ትልቅ የአገር መሪ ባለበት መድረክ የምናገረው ይህን ነው። አዲስ ዘመን፡- ክለቦች በውጭ ተጫዋቾች የሚማረኩትና ከፍተኛ ወጪ የሚመድቡት ከአገር ባለፈ በአህጉራዊ መድረኮች ውጤታማ ለመሆን ነው የሚለውን ይስማሙበታል? ረዳት ፕሮፌሰር ወንድሙ፡- በርካታ ገንዘብ ከመንግሥትና ህዝብ ካዝና እየወጣ ውጤት ቢኖር መልካም ነበር። ይሁንና ክለቦቻችን በአገር ውስጥም ሆነ በአህጉራዊ መድረኮች እየተሸነፉ ከመመለስ በስተቀር ውጤታማ መሆን አልቻሉም። ከፍተኛ ወጪ እያደረጉ የውጭ ተጫዋቾች ማምጣት ለክለቦቹ ውጤት መሻሻል አስተዋጽኦ ቢኖራቸው ኖሮ አይከፋም። ይህ አሠራር እንዳውም የአገር ውስጥ ተጫዋቾች በተለይም ታዳጊዎች እንዳይጎለብቱ እያረገ ነው። ይህ ችግር ከታች ጀምሮ በብዙ ውጣ ውረድ በየደረጃው ለሚገኙ ክለቦች ለሚበቁ የአገር ውስጥ ተጫዋቾች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ማነቆ ሆኗል። ለወደፊቱ የአገሪቱ ስፖርት ምሰሶ የሆኑ ታዳጊዎችና ተተኪ ተጫዋቾች ከመንገድ እንዲቀሩ እያደረገ ነው። በእርግጥ ተጫዋቹ ምርጥ ሊሆን ይችላል። ይህ ምርጥነቱ የሚጠቅመው ግን በክለብ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ብቻ ነው። ኢትዮጵያዊ ባለመሆኑ ብሄራዊ ቡድኑን መወከል አይችልም። ይህም አንዱ የችግሩ ማሳያ ነው። አዲስ ዘመን፡- መንግሥት ክለቦችን ከመደጎም የሚላቀቅበትን የጊዜ ገደብ አለማስቀመጡ ለክለቦቹ የልብ ልብ ሰጥቷቸዋል ይባላል፤ይህን እንዴት ይመለከቱታል? ረዳት ፐሮፌሰር ወንድሙ፡- በእርግጥም መንግሥት ክለቦችን ምን ያህል እየደጎሙ ማቆየት እንደሚቻል ያስቀመጠው የጊዜ ገደብ ላለመኖሩ ዋነኛው ተጠያቂ እንዲሆንና ለችግሩ ዘላቂነት የጎላውን ድርሻ እንዲወስድ ያደርገዋል። ይህን አለማድረጉም፤ክለቦች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ልክ ቀጣይ አደረጃጀታቸውን የሚመለከት አቅጣጫ እንዳይቀይሱና ባሉበት ደረጃ ሁሌም እንዲመላለሱ እያደረገ ይገኛል። ይህ ፈፀሞ ሊስተካከል የሚገባው ነው። መንግሥት ክለቦችን እየደጎመ መቀጠል የለበትም። እየደጎመ የሚያወዳድራቸው ክለቦች ከጥገኝነት ተላቀው ራሳቸውን እንዲችሉ ማድረግ ይገባዋል። ክለቦች የራሳቸውን ገቢ እንዲፈጥሩ መግፋት ይገባዋል። ክለቦች ከመንግሥት ድጎማ ለመፋታት እያደረጉ ያለውን ጥረት መቃኘትና ተግባራቸውን መጠየቅም አለበት። ስፖርቱን ከእኔ እጅ ለመቀበል ምን እያደረጋችሁ ነው እያለ መጠየቅ አለበት ። ከዚያም ክለቦቹን ከመደጎም የሚርቅበትን የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ ይኖርበታል። ከሞግዚትነት መውጣቱን በማሳወቅ በቃኝ ሊላቸው ይገባል። ይህ ካልሆነ ሲደጉም ከመኖር ውጪ ሌላ ፋይዳ የለውም። በአጠቃላይ ክለቦች ከመደጎም፤መንግሥትም ከመደጎም የሚላቀቁበት የመውጫ ስትራቴጂ ሊያዘጋጁም የግድ ይላል። አዲስ ዘመን፡- የክለቦች ወጪና የውጭ ተጫዋቾች ፍላጎትን በሚመለከት ጠንካራ ህገ ደንብ ሊኖረው ግድ ይላል የሚሉ አሉ፤ በዚህስ ላይ ምን ይላሉ? ረዳት ፐሮፌሰር ወንድሙ፡- በእርግጥ የክለቦች የተጋነነ ወጪና የውጭ ተጫዋቾችን በማጋበዝ አንደኛ የመባል ፍላጎትና አቋም ሳይውል ሳያድር መታረም ይኖርበታል። ለዚህም ህግና ስርዓት ያስፈልጋል። እግር ኳሱና ክለቦች የሚተዳደሩበት፤የውጭ ተጫዋች ለምንና መቼ ይምጣሉ፤አመጣጣቸውስ እንዴት መሆን አለበት፤የሚለው በህግና ስርዓት ሊመራ ይገባል። አዲስ ዘመን፡- በአጠቃላይ የአገሪቱን ከለቦች አደረጃጀትና የተጋነነ ወጪ ለማስተካከል ምን መደረግ አለበት? ረዳት ፕሮፌሰር ወንድሙ፡- ከሁሉ አስቀድሞ የክለቦች አደረጃጀት ህዝባዊ መሰረትን የተከተለ እንዲሆን ማድረግ ለነገ የሚባል የቤት ሥራ መሆን የለበትም። ክለቦችም በራሳቸው ቆመው በትክክለኛው መንገድ መራመድ መጀመር ይኖርባቸዋል። አጋጣሚዎች መጠቀምና ደጋፊነትን በሀብትነት መጠቀም ከተቻለ አሁን መልካም ነገሮች ይታያሉ። ክለቦች ከነማ በሚል ተቋቁመዋል። ይህም ህዝብ ለማስገባትና ባለቤታቸው እንዲሆን መልካም መንገድን ይጠርጋል። የፋይናንስ ምንጭ ህዝብ እንዲሆን በማድረግም ክለቦች እየጎለበቱ እንዲሄዱ ያግዛል። ይህ ሲሆን በስፖርቱ ራሱን ለማስተዋወቅ ፍላጎት ያለው ኢንዱስትሪን መጋበዝ ይቻላቸዋል። ይህን ማሳካት ሲችሉም፤ ከመንግሥት ካዝና እጃቸውን ይሰብስባሉ። ሌላው ዓለም የደረሰበት ለመደርስ የሚያስኬደው መንገድም ይህ ብቻ ነው። በውጭ ተጫዋች ዝውውር ረገድም አንድ ሊታወቅ የሚገባው ጉዳይ ቢኖር የህዝብ ፍላጎትና እርካታ ክለቡ የራሱን ምርጥ ተጫዋቾች በማብቃት ውጤታማ ሲሆን መመልከት ነው። ከክለቡ ባለፈ ለብሄራዊ ቡድን መትረፍና ፕሮፌሽናል ተጫዋቾችን አምርቶ ወደ ውጭ መላክ ሲችል ደስታቸው እጥፍ ይሆናል። ይህ እስከሆነም ህዝብ የሚፈልገውን እውን ለማድረግ የውጭ ተጫዋቾች ላይ መንጥልጠልና ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ ማድረግ መቆም አለበት። በአጠቃላይ የአገሪቱን እግር ኳስና የክለቦችን ህልውና ለማስቀጠል የክለቦቻችን ወጪ ቆም ተብሎ ሊታሳብብት ይገባል። ይህም የአገር አጀንዳ ሊሆን ግድ ይለዋል። አሁን ጥያቄው ሊሆን የሚገባው የማምጣት የመውስድና የጊዚ አይደለም። ጉዳዩ የአገር አጀንዳ ነው። የአገሪቱን ስፖርት እንዴት እናሳድግ የሚል ነው። ለዚህ ቁጭ በሎ ማሰብ፤ ማቀድና ያቀዱትንም ወደ ተግባር ለመለወጥ መሥራት ግድ ይላል። አዲስ ዘመን፡- ላደረጉልን ትብብር እናመሰግናለን፡፡ ረዳት ፕሮፌሰር ወንድሙ፡- እኔም አመሰግናለሁ፡፡አዲስ ዘመን መጋቢት 3/2011በታምራት ተስፋዬ", "passage_id": "51bc6d25892c38d0e469a54132ce3f42" } ]
67136c2f714c453eb600fc0899b09297
03113203decaadfcc71b27a06362f673
ስፖርቱን ለማሻገር ተስፋ የተጣለበት ስትራቴጂክ እቅድ
የስፖርት ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው በእጅጉ እየጨመረ እንደመጣ ይታወቃል። የዓለም አገራት የስፖርት ሴክተሩን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመረዳት ብቻ የሚቆሙ እንዳልሆኑ በዘርፉ ያስመዘገቡት ውጤት ማሳያ ነው። በዓለማችን በበርካታ አገራት ከሌሎች ሴክተሮች ባልተናነሰ መልኩ ለስፖርት ልማቱ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ ስማቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ከማድረግ አልፈው ብዙ ማትረፍ ችለዋል፡፡ ለስፖርት ሴክተሩ ትልቅ ትኩረት መስጠት በማህበራዊ ፋይዳው አምራችና ጤናማ ዜጋን በማፍራት ረገድ ያለውን ውጤት ከመረዳት ይመነጫል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ትላልቅ ውድድሮች በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ከሚገኘው ድል ጀርባ ለአገር ፖለቲካዊ ትርፍ ማጣጣም ማስቻሉንም መታዘብ ይቻላል፡፡ ስፖርተኞች ከውድድር ድል በኋላ የሚያገኙት ረብጣ የሽልማት ገንዘብና የአገር ኢኮኖሚን በማንቀሳቀስ የሚገኘው ትርፍም ቀላል አይደለም፡፡ የስፖርቱን ዘርፈ ብዙ ፋይዳን በጥልቅ በመረዳት የስኬት ማማ ላይ የወጡ እንደ ጀርመን ያሉ አገራትን ማንሳት ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለስፖርት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ረገድ ጀርመን በግንባር ቀደምነት ተጠቃሽ ናት። ይህች አገር ስፖርቱ በጠንካራ የፋይናንስ መሠረት ላይ ማቆም መቻሏ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ መሠረቱን ሳይለቅ መጓዝ የቻለ አደረጃጀት መፍጠሯ ለስኬቷ ምክንያት ተደርጎ ይነሳል፡፡ የጀርመን መንግሥት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ከሚያፈስባቸው ዘርፎች ዋነኛው ስፖርት ሊሆን የቻለውም ለዚህ ነው፡፡ ስፖርት በጀርመን ኢኮኖሚ ውስጥ 2 ነጥብ 2 በመቶ ድርሻ ይይዛል። ስፖርቱን በፋይናንስ አቅም እንዲጎለብት ከማድረግ በተጓዳኝ፤ ጠንካራ አደረጃጀት የተዘረጋለት ነው። በጀርመን የስፖርት ዘርፍ ይህን መልክ መላበሱ ከዘርፉ የሚገኘው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲጎላ ማድረጉ ይነሳል። በኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረትና ውጤት ከሌሎች አገራት አንጻር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ በቀደሙት ጥቂት ዓመታት ለስፖርቱ ቅርብ ከሆኑ ሰዎች፣ ከመንግሥትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት በኩል ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ተገቢ ትኩረት መስጠቷ ይነገራል፡፡ ለስፖርት ዘርፍ በተገቢው ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ አለመሆኑንና የዘርፉ እድገት በቁልቁለት ጉዞ ውስጥ መሆኑም በሌላ ወገን ይነሳል። የስፖርት ሴክተሩ ውጤት አልባ መሆኑ ግን ሁለቱንም ወገኖች እንደሚያስማማ ለመታዘብ ይቻላል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህም በመንግሥት ደረጃ ይኸው እውነታ ታምኖበት እየተሰራ ስለመሆኑ በተደጋጋሚ እየተነገረ ይገኛል። በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የዕቅድ በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እንድሪስ አብዱ፤ በአገሪቱ ባለፉት ሁለት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመናት ዘርፉ ለአገሪቱ ማበርከት ካለበት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጠቀሜታዎች አንፃር በሚፈለገው ደረጃ ላይ አለመገኘቱና ውጤቱም በመላ አገሪቱ ተደራሽነት ላይ ክፍተቶች መኖራቸው እንደታመነበት ይናገራሉ:: ለዚህም የስፖርት ሴክተሩን መሠረታዊ ችግር በተረዳ መልኩ የ10 ዓመት የስፖርት ሴክተር ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እንዲሆን በኮሚሽኑ በኩል እንቅስቃሴ ከተጀመረ መሰንበቱን ያስረዳሉ፡፡ ስፖርቱን ወደፊት ለማራመድ እንቅፋት ከሆኑ መሠረታዊ ምክንያቶች መካከል በዋነኛነት ከአደረ ጃጀት፣ ከፋይናንስ፣ ከሰው ኃይል ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች መሆናቸውን የጠቆሙት የኮሚሽኑ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ እንየው አሊ፤ የ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ የተጠቀሱትን ክፍተቶች በጥናት እንዲመልስ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ያስቀምጣሉ፡፡ ስትራቴጂክ ዕቅዱ አገራዊ የስፖርት ሪፎርምን መነሻ በማድረግ በስፋት የተዘጋጀ መሆኑንም ይገልፃሉ። በመሆኑም በአገሪቷ ቀጣይ የስፖርት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ለውጥና ውጤት ማምጣት እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡ የስፖርት ሴክተሩ ሪፎርም ፕሮግራም ዘርፍን መለወጥ የሚችሉ ብዙ ያመላከታቸው ነጥቦች እንዳሉም ያስረዳሉ። በዚህም ከአደረጃጀት ፣ ከፋይናንስ፣ ከሰው ኃይልና ሌሎችም ጉዳዮች አንፃር ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚቻል ተስፋ የተጣለበት መሆኑን ይጠቅሳሉ፡፡ በሪፎርሙ ላይ የሴክተሩ ችግሮች የተለዩ ሲሆን በተመሳሳይ መፍትሄዎች መመላከታቸውንም ያክላሉ። ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገውና ከስፖርት ሪፎርሙ የሚቀዳው የ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ ዘርፍን የተሻለ እንደሚያደርገውም ያላቸውን እምነት ይገልፃሉ፡፡ አቶ እንድሪስ በበኩላቸው፤ በቀጣይ ዓመት ተግባራዊ የሚደረገው ስትራቴጂክ ዕቅድ ትኩረት ያደረጋቸው አንኳር ጉዳዮች መኖራቸውን በመጥቀስ በሴክተሩ በቀጣይ 10 ዓመታት በትኩረት የሚሰራባቸው ተብለው የቀረቡት ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች እንዳሉ ይናገራሉ:: በመጀመሪያ መንግሥታዊ የስፖርት አደረጃጀቶችን የመፈፀም እና የማስፈፀም አቅም በማጎልበት፤ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን እና የአሠራር ሥርዓቶችን ተግባር ላይ ማዋል ፤ ሕዝባዊ የስፖርት አደረጃጀቶችን በዓለም አቀፍ እና በአገር አቀፍ መስፈርቶች መሠረት ማደራጀት የስትራቴጂክ እቅዱ ትኩረት መሆናቸውን ያስቀምጣሉ:: በሁለተኛ ደረጃ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የማሰልጠኛ ማዕከላት ተደራሽነት፣ ሕጋዊነት እና ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን መሠረት በማድረግ በጥራት የሚገነቡበትን ስልት ሥራ ላይ ማዋል ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን ያስረዳሉ። በአህጉር እና ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች በተፈጥሮ ብቃታቸውን መሠረት በማድረግ አገራችንን የሚወክሉ እና ውጤታማ የሆኑ ተተኪ ስፖርተኞችን በሳይንሳዊ ስልጠናዎች ማፍራት ትኩረት ተደርጎ የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑንም ያብራራሉ፡፡ ስፖርት ለማህበራዊ ልማትና ለአገር ብልፅግና ፣ ለሕዝቦች መቀራረብ ፣ ለገፅታ ግንባታ እና ለቱሪዝም ዕድገት መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ትኩረት ሰጥቶ መስራትም የስትራቴጂክ እቅዱ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው። በስትራቴጂክ ዕቅዱ የተጠቀሱትን አንኳር ጉዳዮች መሠረት አድርጎ የተዘጋጀው ግብ ወደ ተግባር መቀየር ከተቻለም የስፖርት ሴክተሩ ውጤታማ መሆን እንደሚችል እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀብታሙ ሲሳይ፤ በአገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲ ባለፉት ሁለት አስር ዓመታት የተመዘገቡ በርካታ አበረታች ውጤቶች ቢኖሩም የአገራችን የስፖርት ዕድገት ከዕድሜው አኳያ ሲመዘን በሚፈለገው ደረጃ ባለማደጉ ብዙ መስራት እንደሚጠበቅ ያመላክታሉ። በአሁኑ ወቅት መንግሥት ስፖርቱን እንደ አንድ የልማትና ብልፅግና መሣሪያ አድርጎ በመውሰድ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየሰራ እንደሚገኝ የሚናገሩት አቶ ሃብታሙ ፤ የስፖርት ዘርፍ በታሪኩ በዚህ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት እንደማያውቅ ያብራራሉ:: የብሔራዊ የስፖርት ምክር ቤት በኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ሰብሳቢነትና የበላይ ጠባቂነት መመራቱ መንግሥት ለስፖርቱ ሴክተር የሰጠውን ትኩረት እንደሚያሳይም ያስቀምጣሉ፡፡ በመሆኑም የስፖርት ዘርፍን ከትናንት በተሻለ መልኩ ዛሬ ትኩረት በማግኘቱ ዕድሉን በአግባቡ በመጠቀም ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን አርብ ጥር 22/2012ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=26437
[ { "passage": "ላለፉት 60 ዓመታት የብስክሌት ስፖርት በኢትዮጵያ ሲዘወተር ቆይቷል። ይህም በአፍሪካ ቀዳሚ ሲሆን፤ እስከ ኦሊምፒክ (ከአትሌቲክስ ቀጥሎ በርካታ ተሳትፎ የተደረገበት ስፖርት) የደረሰ ተሳትፎም አለው። ይሁን እንጂ እንደ ሌሎች ስፖርቶች ትልልቅ ውድድሮችን የማዘጋጀት እድል አልተገኘም ነበር። በዚህም የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ላለፉት ሦስት ዓመታት ጥያቄውን ሲያቀርብ ቆይቷል። የዘንድሮውን ውድድር ለማዘጋጀት ካመለከቱት አምስት ሃገራት መካከልም ኢትዮጵያ ለመጀመ ሪያ ጊዜ ተመራጭ ለመሆን ችላለች።  በአፍሪካ ብስክሌት ኮንፌዴሬሽን የሚመራው የአፍሪካ ብስክሌት ሻምፒዮና በየዓመቱ የሚካሄድ ሲሆን፤\nየዘንድሮው ለ14ኛ ጊዜ ነው። ያለፈው ዓመት መጨረሻ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ከኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን\nጋር በመወያየትም ከመግባባት ላይ መደረሱን፤ የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ወርቁ ገዳ ይገልጻሉ። በዚህም\nበመንግስት በኩል ላለፉት ስድስት ወራት ዝግጅት ሲካሄድ ቆይቷል። ውድድሩን ለማዘጋጀት አንድ ከተማ መመረጥ ስለነበረበት ፌዴሬሽኑ መስፈርቶችን በማውጣት ሁሉንም\nክልሎች የጋበዘ ሲሆን፤ ፍላጎት ያሳዩት ግን የትግራይና የአማራ ክልል ነበሩ። በመስፈርቱ መሰረትም የአማራ ክልል በመመረጡ ውድድሩ\nበባህርዳር ከተማ እንዲካሄድ መወሰኑን ምክትል ፕሬዚዳንቱ ያስረዳሉ። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ ፌዴሬሽኑ\nእንዲሁም ሌሎች ከሚመለከታቸው አካላት የተወጣጡ ኮሚቴዎችም ተዋቅረዋል። በዚህ መሰረት ወደ ስራ የተገባ ሲሆን፤ ከመጪው መጋቢት 5-እስከ 10 ለሚካሄደው ሻምፒዮና የመንገድ፣\nየሆቴል፣… መረጣ እንዲሁም ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶች ወደ መጠናቀቁ ይገኛሉ። በውድድሩ ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ሃገራት በኮንፌዴሬሽኑ\nበኩል ምዝገባ በማድረግ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ ለተመዘገቡትም ቪዛ የማስተካከል እና ሌሎች ስራዎችን እየተከናወኑ ነው። ከዚህ በተጓዳኝ  በውድድሩ ላይ የሚሳተፉትን ሃገራት ለማበረታታት የኢትዮጵያ አየር መንገድ\nቅናሽ ማድረጉንም ምክትል ፕሬዚዳንቱ ይገልጻሉ።    ውድድሩን ከሌላው ጊዜ ለየት የሚያደርገው የ2020 የቶኪዮ ኦሊምፒክ ማጣሪያ በመሆኑ ነው። ከዚህ\nጋር ተያይዞም በርካታ ሃገራት በውድድሩ ላይ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ይጠበቃል። የአምናውን ውድድር የሩዋንዳዋ ኪጋሊ ያስተና ገደችው\nሲሆን፤ ከ46ቱ የኮንፌዴሬሽኑ አባል ሃገራት 32 የሚሆኑት ነበሩ የተካፈሉት፤ ዘንድሮ ቁጥሩ ከዚህም ይልቃል ተብሎ ይጠበቃል። ውድድሩ አራት ተግባራት አሉት እነርሱም፤ በቡድን የሰዓት ሙከራ፣ በግል የሰዓት ሙከራ፣ የጎዳና\nውድድር እንዲሁም ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው የቅልቅል ውድድር ናቸው። ይህ ውድድር 50 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን፤ ሶስት\nሴት እና ሶስት ወንዶች ርቀቱን እኩል ተካፍለው በቅብብል ይወዳደራሉ።  \nኢትዮጵያ ከአዘጋጅነቷ ባሻገር በውድድሩ ተሳታፊ የምትሆን ሃገር እንደመሆኗ ዝግጅቷን ቀድማ መጀመር\nይኖርባታል። በዚህም መሰረት በታህሳስ ወር የብሄራዊ ቡድን ምልመላ መካሄዱን አቶ ወርቁ ይጠቁማሉ። በሃገሪቷ ውስጥ የሚገኙ ቡድኖች\nበሙሉ ዝግጅት እንዲያደርጉ ፌዴሬሽኑ በመስከረም ወር ጥሪ ያስተላለፈ ሲሆን፤ በታህሳስ ወር በተካሄደው የማጣሪያ ውድድር 190 የሚሆኑ\nብስክሌተኞች ተሳትፈዋል። በድጋሚ በተደረገው ማጣራትም 35 የተሻሉ ብስክሌት ጋላቢዎችን በብሄራዊ ቡድኑ በማካተት ልምምድ እየተደረገ\nይገኛል። እስከ ውድድሩ ድረስም የአንድ ወር ዝግጅት ይኖራቸዋል። የቡድኑ አባላት በውድድሩ በዕድሜ ገደብም ይሁን በተለያዩ ርቀቶች\nበሚካሄዱ ሁሉም ውድድሮች ተሳታፊ እንደሚሆኑም ምክትል ፕሬዚዳንቱ ያረጋግጣሉ። በአፍሪካ አህጉር ኢትዮጵያ በስፖርቱ በቀደ ምትነት የምትነሳ ብትሆንም በመሃል በመቀዛቀዙ ምክንያት\nየተዳከመ መስሎ ነበር። ይሁን እንጂ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በማንሰራራት በአህጉር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ የኦሊምፒክ\nተሳትፎን ጨምሮ ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል። በአምናው ሻምፒዮናም ቡድኑ ሁለተኛ በመውጣት አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል። አሁን ደግሞ\nበራሳቸው አየር ላይ በሚያደርጉት ውድድር የተሻለ ውጤት ሊያስመዘግቡ የሚሉ ብስክሌት ጋላቢዎች እየታዩ መሆኑን ምክትል ፕሬዚዳንቱ\nይጠቁማሉ።  ውድድሩ በመካሄዱ የእርስ በእርስ የባህል ልውውጥ ከማድረግ ባሻገር ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ስለሚኖረው\nመልካም እድል መሆኑን ምክትል ፕሬዚዳንቱ ይጠቁማሉ። ለውድድሩ ከ350-450 የሚሆኑ ልኡካን እንደሚመጡ ይጠበቃል፤ በመሆኑም የባህር\nዳር ህዝብ እንግዳ ተቀባይነቱን እንዲያሳይ እና ውድድሩ እስኪጠናቀቅ ድረስም ትብብር እንዲያደርግም ጠይቀዋል።   አዲስ ዘመን የካቲት 18/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "c9753d73a4fb56fb13dbd94474edd681" }, { "passage": "በ1990 ዓ.ም. በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የስፖርት ፖሊሲ ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባው ይደነግጋል። ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሠራበት አካባቢ በስፖርት እንቅስቃሴ ተሳታፊ የሚሆንበት መንገድ መመቻቸት እንዳለበት ያስቀምጣል። ከመንግሥት ተቋማት እስከ ታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል በየደረጃው ኅብረተሰቡ ለሚሳተፍባቸው መድረኮች ትኩረት በማድረግ ልሂቃን (ኤሊቶች) የሚፈጠሩበት ዕድል እንዳለም ፖሊስው ያመለክታል። በሌላ በኩል አምራች ዜጋ ለመፍጠር፣ የኅብረተሰቡ ማኅበራዊ ግንኙነት የሚዳብርበት፣ ከዚያም ሲያልፍ ዜጎች ጤንነታቸውን ለመጠበቅና ለመዝናናት እንዲሁም አካላቸውን ለማጎልበትና አዕምሯዋቸውን ለማበልጸግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ታምኖበታል። የስፖርት ፖሊሲውን መሰረት በማድረግ የሕብረተሰቡን ተሳትፎ በማስፋት ረገድ እየተሄደበት ያለው መንገድ አጥጋቢ አለመሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በመንግስትም ሆነ በህብረተሰቡ በኩል እንደሚነሳው «ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ የስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ አለበት»በሚል በፖሊሲ ደረጃ ቢቀመጥም ወደ ተግባር ከመለወጥ አንጻር ከፍተኛ ክፍተት መኖሩ ይታመናል። በተለይ በመንግስትና በግል ተቋማት ህብረተሰቡ በሚሰራበት ቦታ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ እድል በመፍጠር ረገድ የፍላጎትም ሆነ የግንዛቤ ክፍተቶች እንዳሉ በስፖርቱ አዋቂዎች በኩል ይነገራል። በተቋማት የስፖርቱን ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳን በመረዳት ስፖርታዊ ክንውኖችን የማዘጋጀት ባህሉ በእጅጉ አናሳ መሆኑም አብሮ ይነሳል። መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በኩል የስፖርቱን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመረዳት የስፖርት ፌስቲቫል የማዘጋጀት ልምድ ባለቤት የሆኑ ተቋማት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ከእነዚህ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫሉ ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ ከመስከረም 26 ጀምሮ ለአስር ቀናት ያክል «የኋላውን እያደስን የወደፊቱን ለመገንባት እንተጋለን »በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል። የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል በ2002 ዓ.ም እንደተጀመረ መረጃዎች ያመላከታሉ ። ኮርፖሬሽኑ በሚያከናውነው የስፖርት ፌስቲቫል፤ አገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲውን ተግባራዊ ከማድረግ ባሻገር በሰራተኞች መካከል መቀራረብን እንደሚፈጥር ታምኖበታል። የስፖርት ፌስቲቫሉ ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን በማፍራት ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ማሳያ መሆኑም ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል አስተባባሪ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጥንፉ ሙጬ፤ የስፖርት ፌስቲቫሉ በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣውን የስፖርት ፖሊሲ መሰረት በማድረግ የተጀመረ መሆኑን ይናገራሉ። ህዝቡ በሚኖርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ማጉላት እንደሚችል መሰረት ባደረገ መልኩ ተቋሙ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑንም ይገልጻሉ። እንደ አቶ ጥንፍ ገለጻ፣ ስፖርት በተለይ ደግሞ በሰራተኞች መካከል እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ፣ ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን ለማፍራት እንዲቻል፣ የሰራተኞችን አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው ግዙፍ መሆኑን ያብራራሉ። በመሆኑም ኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫሉን እነዚህን ውጤቶች መሰረት በማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እንደጀመረ ይናገራሉ። «ፌስቲቫሉ በየሁለት ዓመቱ ቢደረግ የበለጠ ዝግጅት ተደርጎ በጠንካራና ባማረ ሁኔታ ማከናወን ይቻላል »በሚል አስተዳደሩ ወስኖ በየሁለት ዓመቱ ሊካሄድ እንደቻለም ያስታውሳሉ። የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት በዚህ መልኩ በመቋቋም ባለፉት አስር ዓመታትን መጓዝ ችሏል። በስፖርት ክንውኑ ተቋሙ ውጤታማ መሆን ችሏል? ስንል ጥያቄ ሰንዝረናል። አቶ ጥንፍ ባለፉት አስር ዓመታት በነበረው ስፖርታዊ ክንዋኔ ተቋሙ ውጤታማ መሆኑን ይገልጻሉ። በመጀመሪያ ደረጃ አመራሩና ሰራተኛው መልካም የሆነ ግንኙነት እንዲፈጥሩ አድርጓል። እያደረገም ይገኛል። በአካልም፣ በአዕምሮም የበለፀገ ሰራተኛና አመራር እንዲኖር አስችሏል። ጤናማ ሰራተኛ በመፍጠር ረገድ ውጤት ማምጣት ተችሏል። መታወቅ ያለበት ያለ ጤናማ ሰራተኛ የኮንስትራክሽን ስራ የሚታሰብ እንዳልሆነም ያብራራሉ። የስፖርት ፌስቲቫሉ ሠራተኛውም ሆነ አመራሩን የበለጠ የሚያቀራርብ፣ ሠራተኛው ትርፍ ጊዜውን አዕምሮውንና አካላዊ ብቃቱን የሚያዳብርበት፣ ለተቋሙ ያለውን ወገናዊነት የሚያሳይበት፣ በሌሎች ፕሮጀክቶች ከሚገኙ ሠራተኞች ጋር ለመቀራረብና ለመተዋወቅ መንገድ እየከፈተ እንደሚገኝ ይገልጻሉ። እንደ አቶ ጥንፍ ማብራሪያ፤ የዘንድሮ መድረክ ከእስከ ዛሬው ለየት የሚያደርገው የተሳታፊነቱን ኮታ ለአመራሩ አንድ ሶስተኛውን በመስጠት ዋና ሥራ አስፈጻሚውን ሳይቀር ተሳታፊ ማድረጉ ነው። ስፖርት ፌስቲቫሉ ለአመራሩና ለሰራተኛው እኩል እድል ከመስጠት ባሻገር፤ በሁለቱ አካላት መካከል መቀራረብ እንዲፈጠርና የበለጠ ቀረቤታን መፍጠር እንዲያስችል ነው። ይህን በተግባርም ለመመልከት ተችሏል። የዘንድሮው ውድድር ሴቶችን የበለጠ ተሳታፊ እንዲሆኑ አድርጓል። በመድረኩ ያለፉት ዓመታት ጉዞ ሴቶች ቡድን አልነበራቸውም፤ ዘንድሮ ሁለት ቡድኖች ተቋቁመው በመረብ ኳስና በጠረጴዛ ቴኒስ ስፖርቶች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ተደርጓል። «የዘንድሮው ፌስቲቫል ልዩ ገጽታው የለውጥ አስተሳሰቦችን ለማስረጽ ጥረት መደረጉ ነው። በውድድሩ ያሉትን ቡድኖች ስያሜን በዚህ ሁኔታ እንዲቃኙ የተደረገ ሲሆን ስያሜዎቹም አሸናፊ፣ ብቁ፣ ታዋቂ፣ ድንቅ፣ ባለራዕይ እና ተስፋ በሚል እንዲሰየሙ ተደርጓል›› ያሉት አስተባባሪው ከዚህ በተጨማሪም ቀደም ሲል ዘርፎች በቡድን ተደራጅተው እርስ በዕርስ የሚያደርጉት ውድድር እንደነበር ተናግረዋል። አደረጃጀቱ እንደ ኮርፖሬሽን ውህደት ባለማምጣቱ አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር ወድድሩ እየተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩ የበለጠ መቀራረብና ተቋማዊ ስሜት መፍጠር እንደተቻለ በውድድሩ የአምስትና ስድስት ቀናት ቆይታ ወቅት ለመታዘብ ተችሏል። የስፖርት ፌስቲቫሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቋማዊ ፋይዳውን እያሳደገ መምጣቱን የ5ኛው የቤተሰብ ስፖርት ውድድር እያሳየም ይገኛል። አቶ ጥንፍ ኮርፖሬሽኑ ግዙፍና በርካታ ፕሮጀክቶች ያቀፈ እንደመሆኑ በስፖርት ፌስቲቫሉ ሁሉም ፕሮጀክቶች ተሳታፊ እንዲሆኑ በመስራት የስፖርቱን ግዙፍ ፋይዳ በተቋሙ ምሉእ እንዲሆን ለማድረግ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አስቀምጠዋል። በ5ኛው የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ሲሳተፍ ያገኘናቸው በኮርፖሬሽኑ የፋሲሊቲ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ዜናው ደነቀው በበኩላቸው፤ የስፖርት ክንውኑን እንደ ኮርፖሬሽኑ ሁሉ ሌሎች ተቋማት ተግባራዊ ማድረግ ቢችሉ ያለውን ፋይዳ ይናገራሉ። «በእኛ ተቋም ያለውን ተሞክሮ በሌሎች የመንግስትና የግል መስሪያ ቤቶች ተግባራዊ ማድረግ ቢቻል፤ በአገር አቀፍ ደረጃ ተጠቃሚ መሆን ይቻላል። ከስፖርቱ የሚገኘውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማግኘት ይቻላል። በተጨማሪም ኢሊት ስፖርተኞች የሚፈሩበትን አጋጣሚ በማስፋት ረገድ የራሱ የሆነ ድርሻ ይኖረዋል። የአገራችንን ስፖርት በማሳደግ ረገድም የመንግስት ተቋማት ድርሻቸውን እንዲወጡ አጋጣሚውን መፍጠር ይቻላል» ሲል ያብራራል። በኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ከአሰልጣኝነት እስከ ዳኝነት የተሻገረ ተሳትፎን ከመጀመሪያው ጀምሮ ሲያደርጉ እንደነበረ የገለፁልን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ሰራተኛ የሆኑት አቶ አለማየሁ ገብሬ፤ የኮርፖሬሽኑ ተሞክሮን ሌሎች ተቋማት መውሰድ ቢችሉ ያለውን ነጥብ በማሳት ተመሳሳይ ሃሳብ ይጋራሉ። የቤተሰብ ስፖርቱን ከመጠንሰስ እና ቀጣይነት እንዲኖረው ከማድረግ አካያ በተቋሙ የነበሩና ያሉ አመራሮች ትልቅ ድርሻ እንደነበራቸውም ይናገራሉ። የኮርፖሬሽኑ አመራሮች የስፖርት ፌስቲቫሉ ሳይቋረጥ እንዲቀጥል ከማደርግ አኳያ ያሳዩት ቁርጠኝነት በተለይ ደግሞ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው ትልቅ ስራን መስራታቸውን ያስረዳሉ። አቶ አለማየሁ ዋና ስራ አስፈፃሚው ስፖርታዊ ክንውኑ ቀጣይነት ኖሮት በጠንካራ መስመር እንዲጓዝ ከመስራት ባሻገር፤ በውድድሩ ተጫዋች በመሆን የስፖርቱ ተሳታፊ መሆናቸው የሚያስመሰግናቸው መሆኑን ይገለጻሉ። ስፖርቱ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረግ አኳያም አመራሩ ያሳየው ቁርጠኝነት በሌሎች ተቋማት እንደ አርዓያ ሊወስዱት ይገባል ባይናቸው። ኮርፖሬሽኑም በየሁለት ዓመቱ ይህ የስፖርት ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ እንደሚገባው ያስቀምጣሉ። በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል ተሞክሮ በሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት መውሰድ ቢቻል ዘርፈ ብዙ ውጤቶች እንደ አገር ማትረፍ እንደሚቻል መመስከር ይቻላል። ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በህብረተሰቡ ዘንድ ትኩረት እንዲሰጠው ፖሊሲ ከመቅረጽ ባሻገር ተግባራዊ እንዲሆን እንደ ኮርፖሬሽኑ ሌሎች ተቋማት መስራት አለባቸው።አዲስ ዘመን  ረቡዕ ጥቅምት 5/2012ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "6d84cfd7c86d1084995b22e46a54eca8" }, { "passage": "ስፖርቱን ለማስፋፋትና ለማሳደግ ዋንኛ መሠረት እንደሆኑ ይታመናል። ለስፖርቱ መሠረታዊ ለውጥና ውጤታማነት የጀርባ አጥነት እንደሆኑ ይነገርላቸዋል። በተለያዩ የዕድሜ ደረጃዎች አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞችን በዘላቂነት ለማግኘት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩ ይነገራል፤ የታዳጊና ወጣት ሥልጠና ፕሮጀክቶች። ስፖርተኞች በሳይንሳዊ ሥልጠና ታግዘው በክለቦችና በብሔራዊ ቡድኖች ለመሳተፍ ብቁና ውጤታማ እንዲሆኑ የማሰልጠኛ ማዕከላት ወሳኝ ሚና አላቸው። የታዳጊ ወጣቶች የስፖርት ፕሮጀክቶች፣ ስፖርቱን ለማሳደግ ወሳኝ ናቸው። ችሎታ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶች በሳይንሳዊ ሥልጠና ከታገዙ ክለቦችንና ብሔራዊ ቡድንን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል። የታዳጊ እና የወጣት ሥልጠና፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይ የታላላቅ የእግር ኳስ ክለቦች ብቃት ያላቸውን ተጫዋቾችን በማፍራት የስኬት መሠረት ናቸው። ለብሔራዊ ቡድኖች እና ለክለቦች ተተኪ የሚሆኑ ስፖርተኞችን ለማፍራት በታዳጊ ደረጃ ሳይንሳዊ ሥልጠና መስጠት ውጤታማ እንደሚያደርግ ይታወቃል። በኢትዮጵያም መሰል ሥልጠና የሚሰጡ ማዕከላት ወጣቶችን ለማፍራት እየሰሩ ነው። በአገር አቀፍ ደረጃ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ የተቋቋመው የታዳጊ ወጣቶች የሥልጠና ልማት ፕሮግራም፣ በዋናነት ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ግብ በማድረግ እንቅስቃሴ ይደርጋል። ሆኖም በታዳጊ ስፖርት ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤት አለመምጣቱ በስፋት ይነገራል። በዘርፍ አዋቂዎች ሆነ ስፖርቱን በሚመራው አካል በኩል ጭምር ውጤታማ አለመሆናቸውን መተማመን መኖሩን ለማስተዋል ተችሏል። የታዳጊ ወጣቶች ሥልጠና ለስፖርቱ እድገት ዋስትና ተደርጎ ቢታመንም፤ የፕሮጀክቱ ውድቀት ለስፖርቱ ቁልቁለት ጉዞ ምክንያት መሆኑም አብሮ ይነሳል። የስፖርቱ መድህን እንደሚሆን የታመነበት የታዳጊዎች ሥልጠና ምዘና ራሱ ድጋፍን እንደሚሻም በዘርፉ አዋቂዎች በኩል በስፋት ይነሳል። ከዚህ በመነሳት የአዲስ አበባ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ከሰሞኑ ባዘጋጀው መድረክ ውድቀት ያመዘነበት የታዳጊዎች ወጣቶች ምዘና የቁልቁለት ጉዞን የሚያሳዩ ምክንያቶች በዘርፍ አዋቂዎች በኩል በዝርዝር ቀርበዋል። የኮሚሽኑን ጥናት መሠረት አድርገው አስተያየታቸውን የሰጡት የስፖርት ባለሙያው ዶክተር ኤልያስ አቢሻክራህ እንደተናገሩት፤ በስፖርቱ ውስጥ የታዳጊ ወጣቶች ሥልጠና ላይ የተሰራው ሥራ ፍሬ አልባ የሆነው ከሰልጣኞቸ፣ ከአሰልጣኞች፣ ከስፖርቱ አደረጃጀትና አመራር ድክመቶች መሆናቸውን በጥናቱ ተለይቷል። በመጀመሪያ ደረጃ ከሰልጣኞች አኳያ ያለውን ለመመልከት ያህል፤ በሥልጠና ማዕከላቱ የሚመለመሉ ታዳጊዎች በፍላጎትና በጨዋታ ብቻ መሆኑ ስፖርቱን ጎድቶታል። ምክንያቱም ሰልጣኞቹ በሜዳ ላይ ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ ባሻገር ሌሎች ቴክኒካል መስፈርቶችን መሠረት በማድረግ ወደ ሥልጠና ማዕከላት መግባት አለባቸው። ይህን ሳይንሳዊ መንገድ አለመከተሉ የታዳጊ ወጣቶች ሥልጠናዎች ማምጣት የሚገባቸውን ውጤትም ሆነ ለውጥ ማምጣት እንዳይችሉ ማድረጉን ጥናቱ እንደሚያመላክት ይናገራሉ። ከአሰልጣኞች በኩል ደግሞ ሙያተኞቹ በሥልጠና ፕሮግራሞቻቸው ላይ ምንም ዓይነት ራዕይም ሆነ ግብ አስቀምጠው የመስራት ዝንባሌ የላቸውም። ሰልጣኝ ታዳጊዎቹ ከየት ተነስተው ወዴት ለማድረስ እየሰሩ ስለመሆኑም አያውቁትም። የሥልጠና ውድድሮች ጨርሶ እቅድ የላቸውም፡፡ እንዲሁም የሥልጠና የጊዜ ገደብ ከሁለት ዓመት ያልበለጠ መሆኑ ሰልጣኞቹ በቆይታቸው በቂ የሆነ አቅምና እውቅት ይዘው እንዳይወጡ አድርጓቸዋል። በተመሳሳይ የአንድ ሥልጠና ክፍለ ጊዜ በዕድሜ እርከን የተቀመጠ አይደለም፡፡ የሥልጠና ማዕከላቱ የሥልጠና ሥነ ዘዴዎች ሳያስቀምጡ መስራት፤ የሥልጠና ፕሮግራሙ ውጤታማነት የሚለካው በውድድርና በውድድር ብቻ መሆኑ የውድቀቱ መሠረታዊ ምክንያቶች መሆናቸውን ጥናቱን መሠረት በማድረግ ያስቀምጣሉ። ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ደግሞ የውጤት ማጣቱን ከአሰልጣኞች የሙያ ብቃት ችግር ጋር የተያያዘ ነው ይላሉ። ʿየታዳጊ ወጣቶች ሥልጠና በስፖርት ሳይንስ ምሩቅ ባለሙያ አልያም የስፖርት መምህር ይሰጥʾ የሚል መመሪያ አለ። በስፖርት ሳይንስ ዲግሪ ያለው ወይም ያላት አሰልጣኝ መቅጠሩን እንጂ፤ ባለሙያው ስለ ቮሊ ቦል፣ እግር ኳስ፣ አትሌቲክስ ወዘተ የስፖርት ዓይነት ምን ያህል እውቀትና ቅርበት አለው የሚለው ከግንዛቤ የሚገባ አልነበረም። በስፖርት ሳይንስ ብቻ ዲግሪ ምሩቅ ከሆነ የትኛውንም የስፖርት ዓይነት ያሰለጥናል። ይህ ዓይነቱ አካሄድ በታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክቶች ውጤታማነት አሉታዊ ነገር ፈጥሯል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በስፖርቱ የታዳጊ ወጣቶች ሥልጠና ሚናው መኮሰሱን ይስማሙበታል። በስፖርቱ ውስጥ የታዳጊ ወጣቶች ሥልጠና ውጤት ለማጣቱ መሠረታዊ ችግሩ የሥልጠና ማንዋሉ መሠረት ያደረገው የዕድሜ እርከን ችግር ያለበት መሆኑ ነው ባይ ናቸው። እንደ አሰልጣኝ ሰውነት ማብራሪያ፤ ታዳጊዎችና ወጣቶች ሥልጠና አማካኝነት የስፖርት ሳይንስና ተግባራዊ ልምምድ ማግኘት አለባቸው ከተባለ ትክክለኛውን ዕድሜ መሠረት ባደረገ መልኩ ማሰልጠን ይገባል። ትክክለኛ ዕድሜ ከየት ይጀምራል የሚለውን ጥያቄን መመለስ ያስፈልጋል። አንዳንድ አገሮች ከሦስት እስከ አምስት ዕድሜ ባሉ ታዳጊዎች ሥልጠና መስጠት ይጀምራሉ፡፡ ከመሰረቱ ስፖርቱን እንዲያውቁት በማድረግ የተለያዩ የዕድሜ እርከኖችን በመከፋፈል ከታች ወደ ላይ በማብቃት ውጤታማ ይሆናሉ። ለምሳሌ እንደ እነ ስፔን ዓይነት አገሮች ከሁለትና ከሦስት ዓመት ጀምሮ ሥልጠና ይሰጣሉ። በተለይ በእግር ኳሱ ያላቸውን ውጤት መመልከት ስልታቸው ምን ያህል ውጤታማ እንደሆነ ያሳያል። ከዚህ በመነሳት የአገራችንን ነባራዊ ሁኔታ እንዲህ ይታዘቡታል። «የታዳጊ ወጣቶች ሥልጠናን በሌሎች አገሮች ከሦስት እስከ አምስት ዓመት ዕድሜ ባላቸው ሕፃናት ሲጀምር፤ በኢትዮጵያ በዚህ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ልጆች የት እንዳሉም አይታወቅም። ከቤታቸውም አይወጡም። የታዳጊ ወጣቶች ሥልጠናን በእኛ ሀገር ከ13 ዓመት ጀምሮ ሥልጠናውን እንጀምራለን። ፕሮግራሙ ከሌሎች አገራት አኳያ እኛ ስምንት ዓመት ወደ ኋላ ቀርተናል። በትክክለኛው የዕድሜ እርከን ላይ ለመስራት እንሞክር ሲሉ ምክረ ሃሳብ ሰጥተዋል።» አሰልጣኝ ሰውነት ለተነሱት ችግሮች በመፍትሄነት ባቀረቡት ሃሳብ፤ በታችኛው ዕድሜ ላይ የሚገኙ ታዳጊዎችን ልናወጣቸውና የሌሎቹን ሀገራት ተሞክሮ ልንከተል ይገባል። ትውልዱ የታዳጊዎች ጉዳይ ይመለከተኛል ካለ ትኩረት አድርጎ መስራት ይኖርበታል። ትክክለኛውን የዕድሜ እርከን በጠበቀ መልኩ ብቃትና አቅም ያላቸውን ስፖርተኞች በማፍራት ስፖርቱ ከገባበት ቁዘማና የቁልቁለት ጉዞው መንጥቆ ማውጣት ይቻላል። አሰልጣኝ ሰውነት ሥልጠናው ከየትኛው ዕድሜ እንደሚጀመር የስፖርት ምሁራን ጥናት ማድረግ ይገባቸዋል። በእርግጥም ከታዳጊ ወጣቶች ዕድሜ አጀማመር ጋር ተያይዞ እልፍ ጥናቶች ተደርገዋል። ነገር ግን የታዳጊ ሥልጠና ተግባር ተኮር በመሆኑ ቤት ለቤት ተዘዋውሮ ሕፃኑ ምን እንደሚሰራ መመልከት ያስፈልጋል። ምሁራኑ የሚያደርጉት ጥናትና ምርምር የሕፃናቱን አቅምና ፍላጎት አጤኖ ማሰልጠን ውጤት ሊያመጣ የሚችል መሆኑን መዘንጋት እንደማይገባ ነው ያሳሰቡት። ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ለሥልጠና ማዕከላቱም በትክክለኛው መንገድ የሥልጠና ሜዳዎችን፣ ቁሳቁሶችና ሌሎች ድጋፎችን መስጠት ያስፈልጋል። በዚህ መልኩ መጓዙ የሚታየውን ጉድለት ይሞላል፡፡ «ስለ እግር ኳስ እየተነጋገርን ታዳጊዎች ላይ በመስራት ወደ ውጤት ያመጣል የምትሮጠው ለመሮጥ ሳይሆን ለአላማ ሊሆን ይገባል። ስለዚህ የሚሰራው ነገር ለውጤት መሆን ይኖርበታል። በመሆኑም የአላማው ግብ እንዲመታ አስፈላጊውን ድጋፍና ተግባር ተኮር ክትትል ያስፈልጋል። የሥልጠና ማዕከላት ሕፃናትን ሰብስበው መለማመጃ ሜዳ ከሌለ፤ሕፃናትን ሰብስበው ኳስ ካጡ የእግር ኳስ ሜዳ ያላቸው ቡድኖች ይተባበሩ ሲሉ ሃሳባቸውን ቋጭተዋል፡፡ ዶክተር ኤልያስ አቢሻክራህ በበኩላቸው ፕሮጀክቶች የስፖርት መሠረተ ልማቶች እና የማሰልጠኛ ቁሳቁሶች አሟልተው መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠኑ አሰልጣኞች እና ሌሎች ድጋፍ ሰጪ ባለሙያዎችን በመቅጠር ጭምር መሰራት አለባቸው፡፡ በወቅታዊ የሥልጠና ማኑዋሎች፤ ሳይንሳዊ ዘዴዎች የጋራ መመሪያ፣ ራዕይና ግብ በመንደፍ ቢንቀሳቀሱ ስኬታማ ሊሆኑ እንደሚችሉ ይናገራሉ፡፡ ኢንስትራክተር ኤርሚያስ አሽኔ በሰጡት ምክረ ሃሳብ፤ አሰልጣኞቹ ያላቸው ችሎታ ወይም የሥልጠና ብቃት ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ነው። ሳይንሳዊ ሥልጠና በተገቢው መንገድ እንዳይሰጥ እንቅፋት ሆኗል ብዬ አስባለሁ። የሀገራችን እግር ኳስ የይድረስ ይድረስ በመሆኑ ክፍተቱ ሰፊ ነው፡ ፡ ሳይንሳዊ ሥልጠናን ወደ\nተግባር ለመተርጎም ከልጅነት ጀምሮ የሚከናወን ነው። እግር ኳስ ቴክኒክ፣ ታክቲክ፣ የአካል ብቃትና ሥነ ልቦና ዝግጅት ይጠይቃል፡፡ እነዚህ ሁሉ በሥልጠናው ተካተው በተሟላ መልኩ ለወጣቶች መሰጠት አለባቸው፡፡ እስካሁን ድረስ በዚህ ረገድ ምን ያህል ተሰራ የሚለው ጥናት የሚያስፈልገው ቢሆንም ሥርዓቱን ተከትሎ እየሄደ ነው ለማለት አያስደፍርም። በመሆኑም ይሄንን አካሄድ በሚገባ ማስተካከል በመፍትሄነት የሚቀርብ ሃሳብ ነው ባይ ናቸው። የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዮናስ አረጋይ በተነሱት ችግሮችና በተመላከቱት የመፍትሄዎች ሃሳቦች ላይ ተተርስው አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ ኮሚሽኑ የጥናቱን ውጤት ወደ መሬት በማውረድ በስፖርቱ መሠረታዊ የሆነ ለውጥና ውጤት ለማምጣት ጥረት የሚደረግ ይሆናል ሲሉ አመላክተዋል። የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በበቂ ሁኔታ ያለመኖር ለታዳጊ ወጣቶች ሥልጠና ፕሮጀክቶች የሚጠበቅባቸውን ውጤት ያለማምጣታቸው በሌላ ወገን እንደ ችግር ተነስቷል። ኮሚሽኑ ያለውን ችግር እንደሚረዳና መፍትሄ ለመስጠት ሰፊ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ነው ያመላከተው። በተለይ በአሁኑ\nወቅት በከተማ አስተዳደሩ\nበኩል ለዘርፍ ከፍተኛ\nትኩረት በመስጠት ሥራዎች\nእየተሰሩ ይገኛሉ። ስፖርቱ\nከገባበት ቁዘማ ለማውጣት\nጥረት ይደረጋል ሲሉም\nሃሳባቸውን ይሰነዝራሉ። አቶ ዮናስ፤\nየአዲስ አበባ ከተማ\nአስተዳደር ወጣቶችና በጎ ፈቃድ\nማስተባበሪያ ቢሮ የ2011 ዓ.ም\nየበጋ_በጎ_ፈቃድ\nመርሀ ግብር ማጠናቀቂያ\nመርሀ ግብር ለወጣቶች\nዕውቅና በመስጠትና ወደ ክረምት_የበጎ_የፈቃድ\nሥራ ለመግባት የቅድመ\nዝግጅቱን ማጠናቀቁንም አያይዘው\nገልጸዋል።አዲስ ዘመን ሰኔ 12/2011 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "f2d60527383f226bdf97a80cd97fa6ac" }, { "passage": "በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት ከሚዘወተሩ የስፖርት አይነቶቸ በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል ። በተለያዩ አገራት ከፍተኛ ተቀባይነትን ማግኘት የቻለው የዳርት ስፖርት መነሻው ጥንታዊቷ ግሪክ እንደሆነች የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ። በግሪክ ወታደራዊ ተቋማት ውስጥ የዳርት ስፖርት በተለየ ሁኔታ ይዘወተር ነበር። በአጭር ጊዜም በአገሪቱ የሚኖረው ሌላው ማህበረሰብ አውቆት በስፋት ወደ ማዘውተር መሸጋገሩ ይነገራል፤ የዳርት ስፖርት፡ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በስፋት ወደ መዘውተር ሊሸጋገር የቻለውም በዚህ ሂደት ውስጥ አልፎ ነው። ዳርት አካልንና አዕምሮን የሚያነቃቃ ባህሪ የተላበሰ ስፖርት ሲሆን፤ የማሰብ ችሎታን የማሳደግ አቅም ያለው መሆኑ ስፖርቱን ተወዳጅ እንዲሆን አድርጎታል። \nስፖርቱ መነሻውን ግሪክ ያድርግ እንጂ በአሁኑ ወቅት አድማሱን በማስፋት በተለያዩ አገራት በመዘውተር ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ስፖርቱ መዳረሻውን ካደረገባቸው አገራት መካከል አንዷ ናት። ስፖርቱ በአገሪቱ መዘውተር ከጀመረ ረጅም ጊዜ እንዳስቆጠረም መረጃዎች ያመላክታሉ። የስፖርቱ መዘውተር የጀመረበት ዓመታትን ያስቆጠረ ቢሆንም በሚፈለገው የዕድገት ደረጃ ላይ እንደማይገኝ ይስተዋላል። ስፖርቱ ዕድሜ፣ ጾታ፣ ሃይማኖት፣ የዘርና ቀለም ልዩነት ሣይገድበው ማንኛውም ሰው አካሉንና አዕምሮውን ለማዳበር፤ ጤናውን ለመጠበቅ፣ በመስኩም ተወዳዳሪ ለመሆን የሚሳተፍበት ስፖርት ቢሆንም፤ በሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች እየተዝወተረ እንደማይገኝ ለስፖርቱ ቅርብ የሆኑ ሰዎች ወቀሳ ሲሰነዝሩ ይስተዋላል። ለዳርት ስፖርት እንደሌሎች የስፖርት አይነቶች ትኩረት አለመሰጠቱም ምክንያት ተደርጎ ይነሳል። \nየኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን ጽፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጥላሁን አላምረው፤ ስፖርቱ በሚፈለገው ደረጃ እንዳያድግ ከበጀት እጥረት ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውን ይናገራሉ። ይህም ስፖርቱን በብዙ መልኩ ጎድቶታል። የኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን የዓለም አቀፍ ዳርት ፌዴሬሽን (WDF) አባል መሆኑን ተከትሎ እ.ኤ.አ በ2017 በጃፓን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ኢትዮጵያ የመሳተፍ ዕድሉን አግኝታ ነበር። ለአገራችን የዳርት ስፖርት ይህ አጋጣሚ ትልቅ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ባለበት የበጀት ውስንነት ምክንያት ብሔራዊ ቡድኑን በዚህ መድረክ ላይ ለማሳተፍ ሳይቻል መቅረቱን እንደ ማሳያ ያስቀምጣሉ። \nበአገሪቱ የዳርት ስፖርት በሚፈለገው ደረጃ እንዳይጓዝ የተለያዩ ፈተናዎች እንቅፋት ቢሆኑበትም፤ ፌዴሬሽኑ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየሠራ መሆኑን አቶ ጥላሁን ያነሳሉ። ስፖርቱን ከማስተዋወቅ፣ ከማስፋፋት አኳያ በርካታ ሥራዎችን በተለየ መልኩ በማከናወን ውጤታማ መሆንም እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ለዚህም በአገር አቀፍ ደረጃ የውድድር መድረኮችን እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አማራጭ ተደርጎ እንደተወሰደም ያመለክታሉ። ለአብነትም በኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን አማካኝነት የሚዘጋጀው አገር አቀፍ የዳርት ቻምፒዮና ስፖርቱ በህብረተሰቡ ዘንድ ተወዳጅና ተዘውታሪ እንዲሆን ባለፉት ዓመታት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። \nበአገር አቀፍ ደረጃ፣ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የሚሳተፉበት ዓመታዊ የዳርት ቻምፒዮና ስፖርቱን ከማስተዋወቅ፣ ተወዳጅና ተዘወታሪ ከማድረግ ባሻገር ታዋቂ ስፖርተኞችን ከማፍራት አኳያ አበረታች ውጤትም ማግኘት መቻሉን አብራርተዋል። የውድድር መድረኩ ለስፖርቱ ውጤታማነት ያለውን አስተዋጽኦ ለመጨመር በዘንድሮው ዓመትም ቻምፒዮናው የሚቀጥል ይሆናል። የኢትዮጵያ ዳርት ቻምፒዮና ለ14ኛ ጊዜ በመጪው ሰኔ በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ ለማካሄድ ዝግጅት\n ሲደረግ የቆየ ሲሆን፤ በዓለም ዓቀፍ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ሻምፒዮናው ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ነው ያመላከቱት። \nብሔራዊ ፌዴሬሽኑ የስፖርቱን እንቅስቃሴ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንዲህ አይነት ውድድሮችን በማዘጋጀት የሚወሰን አለመሆኑን ያነሳሉ። በማንኛውም ደረጃ የሚካሄዱ የዳርት ውድድሮች፣ ግጥሚያዎችና ጨዋታዎች ወጥ በሆነ መንገድ የሚመሩት ሥራዓቶችን በማበጀት እየተሰራ ይገኛል። ስፖርቱን ትክክለኛውን መስመር እንዲይዝ የሚያደርገውን ማንዋሉ በዘርፉ ባለሙያዎች በተዘጋጀና ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎችን ባካተተ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑ ውጤቱ የተሻለ እንዲሆን ያደርገዋል ሲሉ አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ ስፖርቱ ተወዳጅ ቢሆንም፤ እየተኬደበት ያለው መንገድ መሰናክል የበዛበት መሆኑን በመጨረሻ ያነሱት፤ ኃላፊው፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኑም በቀጣይ የውድድር አማራጮችን መፍጠር ያስፈልጋል። በመሆኑም የዳርት ስፖርትን የበለጠ ተወዳጅና ተዘውታሪ ከማድረግ፣ ከማዘመን፣ ስፖርታዊ ጨዋነትን ከማስፈን፣ የመረጃ አያያዝ ሥርዓትን ከማቀላጠፍ፣ በክልል ፌዴሬሽኖች፣ ማህበራትና ሌሎች ክበባት መካከል የጋራ ግንዛቤን ከማዳበር አንፃር ሰፊ ሥራዎቸን ለመሥራት ዕቅድ መያዙን አስታውቀዋል። የዓለምን ህዝብ ሥጋት ውስጥ የከተተው የኮሮና ቫይረስን በመቆጣጠር በሀገራችን መደበኛ እንቅስቃሴ መጀመር ሲቻል ፌዴሬሽኑ እነዚህና መሰል ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሠራ በማስገንዘብ ሐሳበቸውን ቋጭተዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 13/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "c7490cbc30ca4cde47f18370fb5ddfa6" }, { "passage": " ለብሄራዊ ቡድኖች እና ለክለቦች ተተኪ የሚሆኑ አትሌቶችን ለማፍራት በታዳጊ ደረጃ ስልጠና መስጠት ውጤታማ እንደሚያደርግ ይታወቃል። ከፕሮጀክቶች የተሻለና የላቀ ችሎታ ያላቸው ታዳጊዎች ሳይንሳዊ ስልጠና አግኝተው ክለቦችንና ብሄራዊ ቡድንን ለመቀላቀል ብቁ እንዲሆኑም የማሰልጠኛ ማዕከላት መኖር ወሳኝ ነው። በኢትዮጵያም ውስን ማዕከላት ተከፍተው ወጣቶችን ለማፍራት እየሰሩ ይገኛሉ።የአትሌቲክስ ስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላቱ በትግራይ ክልል ማይጨው፣ በአማራ ክልል ደብረ ብርሃን፣ በኦሮሚያ ክልል በቆጂ እንዲሁም በደቡብ ብሔር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ሃገረ ሰላም ላይ የተገነቡ ናቸው። በ2000ዓም ወደ ሥራ የገቡት እነዚህ ማዕከላት በተለየ መልኩ ሊመረጡ የቻሉትም ለአትሌቲክስ ስፖርት ምቹ የሆነ የቦታ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ስላላቸው ነው።የስፖርት ማዕከላቱ ከተቋቋሙ በኋላም ለሚገኙባቸው ክልሎች በኃላፊነት ተሰጥቷል። ይሁን እንጂ ማዕከላቱ በእርስ በእርስ የመማማሪያ መድረክ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት በክልሎቻቸው የሚያገኙት ድጋፍ የተለያየ መሆኑ ነው ለማስተዋል የተቻለው። አንዳንድ ክልሎች ድጋፍ በማድረጋቸው የተሻለ ሥራ ሲያከናውኑ አንዳንዶች ደግሞ ድጋፍ ስለማድረጋቸውም በሚያጠራጥር ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም ክልሎች ለማዕከላቱ የሚያደርጉት ድጋፍ ምን ይመስላል የሚለውን መመልከት ይገባል።ተሞክሯቸውን ካቀረቡት ማዕከላት መካከል በተሻለ ደረጃ ላይ የሚገኘውና እነደ ተምሳሌትም ሲታይ የነበረው የሃገረ ሰላም አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ነው። በደቡብ ስፖርት ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር አቶ እስራኤል ቡአ፤ ኮሚሽኑ ከማዕከሉ ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ይገልጻሉ። በማዕከሉ በሚደረገው ክትትልና ድጋፍ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት እንዲሁም የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በረጅም፣ አጭርና መካከለኛ ጊዜ ምላሽ ይሰጥበታል። ያለ ጥሬ ዕቃ ስልጠናውን ማስኬድ የማይቻል በመሆኑም፤ በመንግሥት ተገቢው ትኩረት እንዲሰጠውና በቂ በጀት እንዲመደብለትም በቅንጅት ይሰራል።ከዚህ ቀደም በማዕከሉ የሚገኘው የወንድና ሴት ሰልጣኞች መኖሪያ በአንድ አካባቢ የሚገኝ መሆኑን ተከትሎ ማስፋፊያ በማድረግ ለማለያየት ተችሏል። ኮሚሽኑ ማስፋፊያውን ከማድረጉም ባሻገር 1ነጥብ6 ሚሊዮን ብር ለካሳ መክፈሉንም ነው የሚገልጹት። ከዚህ ባለፈ በቤንቺ ማጂ እና ደቡብ ኦሞ ዞን የራሱን የታዳጊ ማሰልጠኛ ተቋም በመገንባት ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ አንዱ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝም ነው ዳይሬክተሩ የሚገልጹት።ማዕከሉ ከምልመላ ጀምሮ መስፈርቱን ተከትሎ ሥራው በጥንቃቄ እንዲካሄድ ለማድረግም ኮሚሽኑ ክትትል ያደርጋል። የምልመላ ቡድኑ ወደ ተለያዩ ሥፍራዎች ሲንቀሳቀስ ጥብቅ መመሪያ የሚሰጥ ሲሆን፤ ሲመለስም ክትትሉ የሚቀጥል ይሆናል። ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ እና ኮሚሽኑ ጋር ተገቢ መናበብ ቢኖርም አልፎ አልፎ አንዳንድ ገባ ወጣ ማለቶች ይስተዋላሉ፤ ግምገማ በማካሄድም ለማስተካከል ጥረት ይደረጋል።ክልሉ ያለፈው ዓመት ሊካሄድ ለነበረው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች በጀት ቢመድብም፤ ውድድሩ ግን በሀገር አቀፍ ደረጃ አልተካሄደም ነበር። በመሆኑም ገንዘቡን ለማዕከሉ የጂምናዚየም ቁሳቁስ ግዢ ለማዋል ተችሏል። ይሁን እንጂ ከመብራት ኃይል ጋር ተያይዞ አገልግሎት መስጠት ያልጀመረ ሲሆን፤ በቅርቡ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር ሥራ እንደሚጀምርም ነው ዳይሬክተሩ የሚጠቁሙት።ሀገራዊና ወጥ የሆነ የአሰራር መመሪያ በማዕከላቱ የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ያስችላል። የልምድ ልውውጥ መድረኩን መካሄድ ተከትሎም የአሰራርና አደረጃጀት መመሪያ የሚዘጋጅ በመሆኑ፤ የሰልጣኞች ሽግግርና ዝውውር ላይ የሚፈጠሩ ችግሮችን የሚመልስ መመሪያ ይበጃል ብለው እንደሚጠብቁም ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ።በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት ታሪክ ሰፊውን ድርሻ የሚይዙት ውጤታማ አትሌቶች ከበቆጂ የተገኙ መሆኑ ይታወቃል። በዚሁ ምክንያትም አካባቢው በዓለም ደረጃ «የሯጮች ምድር» እስከመባል ደርሷል። በዚህ ወቅትም በርካታ የረጅም ርቀት አትሌቶች ከአካባቢው እየወጡ ይሁን እንጂ ከስሙ አንጻር የበቆጂ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል በሚጠበቀው ልክ በመስራት ላይ ይገኛል ለማለት አያስደፍርም። ከአትሌቲክስ ማዕከል ባሻገር የፊፋ ጎል እግር ኳሰ ማሰልጠኛ ፕሮጀክት የሚገኝ መሆኑም ይታወቃል።የክልሉ ስፖርት ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር አቶ ግርማዬ ለታ፤ ማዕከላቱ ከውጤት አንጻር ሲመዘኑ እንደሚጠበቀውም ባይሆን ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ይገልጻሉ። ይህ ሊሆን የቻለው ደግሞ ባለድርሻ አካላት፤ ስፖርት ኮሚሽን፣ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ ፌዴሬሽኑ እንዲሁም የክልል ቢሮዎች እኩል ትኩረት ሰጥተው በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ ባለመሆኑ ነው። ማዕከላቱን በማሰባሰብ ተሞክሯ ቸውን በመቅሰም እርስ በእርሳቸው ልምድ እንዲለዋወጡ ማድረግ የተለመደ ባለመሆኑም የሰሩተን ስራ በትክክል ማቅረብ ላይ ችግር አለ።ኮሚሽኑም በአካባቢው የተሻለ ሥራ እንዲሰራ ባለሙያዎችን የማብቃትና የሙያ ማሻሻያ እንዲያገኙ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ይጠቁማሉ። ለማዕከሉ ጽህፈት ቤት በመስጠት፣ በጀት በመመደብ፣ ጂምናዚያም እንዲሁም የሁለቱን ማዕከላት መዋቅር በመከለስ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሰራም ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። ትኩረት እየተሰጠ አይደለም ይባል እንጂ ከሌሎች ክልሎች የተሻለ በጀት በመመደብና ትኩረትም በማድረግ ላይ ይገኛል። በዚህም ካሉት ማዕከላት በተጨማሪ አንድ ቢሊዮን በሚሆን ወጪ ሱሉልታ ላይ በርካታ ስፖርቶችን የሚያሰለጥን አካዳሚ በመገንባት ላይ እንደሚገኝም በማሳያነት ያነሳሉ።የማሰልጠኛ ማዕከላቱ እና አካዳሚው ተመሳሳይ ሥራ የሚሰሩ ቢሆንም በሀገር አቀፍ ደረጃ ግን ትኩረት አልተሰጠውም። መሆን የሚገባው ግን አንዳቸው ከሌላው በተለየ የረጅም ጊዜ እቅድ በመያዝ የተሻለ ነገር ላይ ማተኮር ነው። እንደ ክልል ግን ያሉትን ነገሮች በማየት በተሻለ መልክ እንደሚካሄድበት ነው የሚገልጹት።የትግራይ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የትምህርትና ስልጠና ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ከሃሳይ ፍሰሃ፤ የማይጨው አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ከተመሰረተበት 2002ዓ.ም ጀምሮ እድገት በማሳየት ላይ ያለ መሆኑን ይጠቁማሉ። ቢሮው ጅምናዚየም በማስገንባት፣ የሰልጣኞችን ቁጥር ከ35 ወደ45 በማሳደግ እንዲሁም በጀት በመመደብ ቢሮው ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ይገልጻሉ።ማዕከሉ የራሱ ስታንዳርድ የሌለው ሲሆን፤ አንድ ማዕከል ምን ምን መያዝ አለበት የሚለው፣ እንዲሁም ወደየት ማደግ አለበት በሚለው ላይ ስታንዳርድ አልነበረውም። ከሌሎች የታዳጊ ስፖርት ማሰልጠኛ ፕሮጀክቶች ጋርም ትስስር አልነበረውም። በመሆኑም በምን መልኩ መዋቀር ይገባዋል በሚለው ላይ ቢሮው ጥናት እያደረገ ይገኛል። ጥናቱ ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባም ችግሮቹን ይፈታል ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንም፤ ከነችግሮቹ ሰልጣኞችን ወደ ተለያዩ ክለቦች በመመገብ ሀገርን ወክለው በውድድሮች ላይ የሚካፈሉ አትሌቶችን ማፍራት ችሏል። የማዕከል ቆይታቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞችም ወደ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ፣ ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከል እንዲሁም በክልሉ የሚገኙ ክልሎችን እንደሚቀላ ቀሉም ባለሙያው ይጠቁማሉ።ሊተኮርበት የሚገባውም ማዕከላቱ በየራሳቸው ከሚያደርጉት ጥረት ይልቅ ኮሚሽኑ ወጥ የሆነ መዋቅር ቢሰራ የተሻለ እንደሚሆንም ይጠቁማሉ ባለሙያው። ይህ ሲሆንም ክልሎች ማሟላት የሚገባቸውን አውቀው ሥራቸውን ያከናውናሉ። በዚህም ስፖርቱን ለማሳደግ እንደሚችልም እምነታቸው ነው።በአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን የተሳትፎ፣ ስልጠና ውድድር ዳይሬክተር አቶ ምትኩ አክሊሉ፤ በክልሉ በሚገኘው የደብረ ብርሃን አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል አስተያየታቸውን ይሰጣሉ። አሁን ባለበት ሁኔታ እንዲሁም በሚያፈራቸው አትሌቶች አንጻር ሲታይ ጥሩ ሥራ እየሰራ ይገኛል ለማለት እንደሚያስደፍር ይጠቁማሉ። በፓራሊምፒክ ስፖርትም ማዕከሉን እንዲጠቀሙት በማድረግ ላይ ይገኛል። የደብረ ብርሃኑን ተሞክሮ በመያዝ መሰል ማዕከልም በሌሎች ዞኖች ላይ በማደራጀት ጥረት ላይ አንዳሉም ይገልጻሉ።ክልሉ በየዓመቱ ከሁለት ሚሊዮን ብር ያላነሰ ድጋፍ ያደርጋል። ይሁን እንጂ ክልሉ ትኩረት በመስጠት በኩል የሚጠበቅበትን እንዳላደረገም ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። ከዚህ በኋላም ክልሉ ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ችግር ባለበት የሽግግር ሥርዓት ላይ የአሰራር ማኑዋል በማዘጋጀት ወጥ በሆነ መንገድ መስራት ይገባል። በቀጣይም ማሰልጠኛ ማዕከላት አንድን ስፖርት ብቻ መሰረት አድርገው ሳይሆን ቀስ በቀስ ሌሎች ስፖርቶችንም ማካተት እንደሚገባ ከመድረኩ ተሞክሮ ለማግኘት እንደቻሉም ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። በመሆኑም በቀጣይ የቀሩትን ሥራዎች በማከናወን በኩል ከክልሉ በርካታ ነገር የሚጠበቅ ይሆናል።አቶ ሲሳይ ሳሙኤል በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር፤ በመድረኩ ላይ በርካታ ጉዳዮች መነሳታቸውን ይጠቁማሉ። የመጀመሪያው ነገር በአስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ የታየ ጉድለት ነው። ይህም ወጥ የሆነ አሰራርና መመሪያ በማበጀት ማዕከላቱ ተመጋጋቢ እንዲሆኑና ውጤታማ አትሌቶችን ለማፍራት ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑ ታይቷል። ችግሩን የመቅረፍ ኃላፊነት የኮሚሽኑ ሲሆን፤ ተግባራዊነቱ ላይ ደግሞ ክልሎች ኃላፊነቱን መውሰድ እንዳለባቸውም ያሳስባሉ። ከዚህ በኋላም ይህ ዓይነት መድረክ በማይቋረጥ መልኩ የሚካሄድም ይሆናል።አዲስ ዘመን ጥር 13/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "68aec4e5929fca4954c60ff2e1cea7e4" } ]
cbbf8647719ec7339913803274b05b60
3a8f26005617a2af28416a8466fa1786
የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተራዘመ
የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በቻይና የሚካሄደውን የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር ማራዘሙን አስታወቀ። እአአ ከመጋቢት 13 እስከ 15 ቀን 2020 በቻይና ናጂንግ ከተማ ሊካሄድ የነበረው 18ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክውድድር ለ12 ወራት ያህል እንዲራዘም መደረጉን የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ዋቤ አድርጎ ቢቢሲ ዘግቧል። የዓለም አትሌቲክስ የጤና ቡድን ከዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ጋር በቻይናና ከቻይና ውጪ በሌሎች አገራት የኮሮኖ ቫይረስን አስመልክቶ በቅርበት መረጃዎችን በመለዋወጥ ባገኘው መረጃ ኮሮና ቫይረስ አሳሳቢ ደረጃ ላይ የሚገኝ እንደሆነ ለመረዳት መቻሉን ዘገባው አመልክቷል። በቻይና መነሻውን ያደረገው ኮሮና ቫይረስ 130 ሰዎችን የገደለ ሲሆን፤ በ16 ሀገራት ተስፋፍቷል። ከስድስት ሺህ ሰዎች በላይም በቫይረሱ መጠቃታቸውን ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ በመነሳት የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቻይና በተስፋፋው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት ውድድሩን በተባለለት ጊዜ ማካሄድ አስቸጋሪ መሆኑን በማመን ውድድሩ እንዲራዘም ውሳኔ አሳልፏል። በመሆኑም እ.አ.አ በ2021 ውድድሩ እንዲካሄድ አማራጭ መቅረቡን አስታውቋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል። የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድሩን በሌሎች አገራት ለማድረግ አስቦ እንደነበር ያስታወቀው ፌዴሬሽኑ ቫይረሱ ከቻይና ውጪ ወደ ሌሎች አገራት የመሰራጨቱ ጉዳይ አሳሳቢ ስለሚሆን አገር የመቀየር ምርጫውን መሰረዙን አመልክቷል። ብዙ አትሌቶች ውድድሩ እንዲካሄድ ካላቸው ፍላጎት አንጻርም የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድሩን ሙሉ ለመሉ የመሰረዝ ምርጫውንም እንደተወውም ነው ተጠቀሰው። ይህ በመሆኑ ምክንያት ናንጂንግ እ.አ.አ በ2021 ውድድሩን የሚካሄድበት ምቹ ጊዜ ማግኘት እንደምትችል የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል። የዓለም አትሌቲክስ ከአትሌቶች፣ ከናንጂንግ የውድድር አዘጋጅ ኮሚቴና ከአጋሮች ጋር የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድር እ.አ.አ 2021 የሚካሄድበት ቀን ለመወሰን በቅርበት እንደሚሰራም አስታውቋል። የዓለም አትሌቲክስ ቻይና የኮሮኖ ቫይረስን ለመከላከል እያደረገች ያለችውን ጥረት እየተከታተለ እንደሆነና ተቋሙ አገሪቷ እያከናወነች ላለው ሥራ ድጋፍ እንደሚያደርግም ቃል መግባቱንም አስፍሯል። ቫይረሱን አስመልክቶ ለአትሌቶች፣ ለብሔራዊ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖችና አጋሮች በፍጥነት እየተለዋወጡ ያሉ ጉዳዮችን ማሳወቅ ተገቢ እንደሆነም ማመልክቱን ቢቢሲ ዘግቧል። የእስያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በየካቲት ወር 2012 ዓ.ም በቻይና ሀንግዙ ግዛት ሊካሄድ የነበረውን ዘጠነኛው የእስያ የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድር መሰረዙን ከአራት ቀናት በፊት ማስታወቁ ይታወሳል።አዲስ ዘመን አርብ ጥር 22/2012ዳነኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=26439
[ { "passage": "ዓለምን በውዥንብር ውስጥ የከተታት የኮሮና ቫይረስ በተለይም መዝናኛውን ጥላ አጥሎበታል፡፡ የቻይና እግር ኳስ ሊግን በማቋረጥ መዝናኛውን መረበሽ የጀመረው የኮሮና ቫይረስ ሰሞኑን ደግሞ ወደጣሊያን ተሻግሮ የጣሊያን ሴሪ ኤን እንዲራዘም አስገድዷል፡፡ የጣሊያን ሴሪ ኤ ጨዋታዎች ያለ ደጋፊ በመቅረብ ደብዝዘውም ነበር፡፡ይኼው ስጋት በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ላይ መጣል ጀምሯል፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በ29ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታዎች ተጫዋቾች ወደሜዳ ሲገቡ ከተቃራኒ ቡድን ተጫዋቾች እና ከዳኞች ጋር እንዳይጨባበጡ ተደርጓል፡፡በመጪው መጋቢት የመጨረሻ ሳምንት በቻይና ሊካሄደው የነበረው የጊዲኒያ የዓለም የግማሽ ማራቶን ለጥቅምት 7 ቀን 2013ዓ.ም መዛወሩን የዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን\nበታርቆ ክንዴ", "passage_id": "f1d03c48f2d6200639e0a4f84524aad6" }, { "passage": "በኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት የስፖርቱ ዓለም ካለፉት ሁለት ወራት በላይ እንቅስቃሴው ተገድቦ ቢቆይም ከቅርብ ቀናት ወዲህ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ለመመለስ ሲፍጨረጨሩ እየተስተዋለ ነው። ታላላቆቹን አውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች ጨምሮ አንዳንድ አገራትም ስፖርታዊ ውድድሮቻቸውን ለማስጀመር ከቫይረሱ ስጋት ነፃ ሳይሆኑ ጥረት እያደረጉ ሲሆን አብዛኞቹን ውድድሮች በዝግ ስቴድየሞች በማድረግ የውድድር ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት መርሐግብሮቻቸውን ስለመፈፀም እየተጨነቁ ይገኛሉ። \nበርካቶቹ የዓለም አቀፍ ውድድሮች ግን ቀደም ሲል ቫይረሱ በቀጣዩ ዓመት ይጠፋል ወይም በቁጥጥር ስር ይውላል በሚል ተስፋ ወደ ቀጣይ ዓመት እንዲዞሩ መወሰናቸው ይታወሳል። ከእነዚህ መካከል በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዘግይቶም ቢሆን በቫይረሱ ስርጭት ስጋት የተነሳ ታላቁን የስፖርት መድረክ ለአስራ ስድስት ወራት እንዲራዘም ማድረጉ ይታወሳል። ይህም እንደሌሎቹ ውድድሮች ሁሉ ቫይረሱ በቀጣዩ ዓመት በቁጥጥር ስር ይውላል ከሚል ተስፋ እንጂ በተጨባጭ መረጃና ማስረጃ አልነበረም። በርካቶቹ ይህን ተስፋ የሙጥኝ ብለው እያንዳንዱ ቀን እንደ ዓመት እየረዘመባቸውም ቢሆን ቀጣዩን ዓመት በጉጉት እየተጠባበቁ ይገኛሉ። የቫይረሱ ስርጭት ግን በተቃራኒው እየቀነሰ ከመሄድ ይልቅ በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል። እስካለፈው ማክሰኞ ድረስም በዓለም ላይ ከ625 ሺህ በላይ ኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) የተገኘባቸው ሰዎች ሲያገግሙ የተጠቂዎች ቁጥር ወደ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን አሻቅቧል። የ165 ሺ 235 ሰዎች ሕይወትም በቫይረሱ ተቀጥፏል። ይህም ቁጥር በየደቂቃው እያሻቀበ ይገኛል። \nይህንን ያስተዋሉ የጤና ባለሙያዎችም ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በቀጣዩ ዓመት ላይካሄድ እንደሚችል ከወዲሁ እየተናገሩ ይገኛሉ። የኦሊምፒኩ አዘጋጅ የሆነችው ጃፓን የተላላፊ በሽታዎች ፕሮፌሰር የሆኑት ኬንታሮ ዋታ የቫይረሱ ስርጭት ኦሊምፒኩ በተራዘመበት ወቅት በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ አጠራጣሪ በመሆኑ ውድድሩ ላይካሄድ እንደሚችል ስጋታቸውን ለመገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል። \n‹‹እውነቱን ለመናገር ኦሊምፒኩ በቀጣዩ ዓመት ይካሄዳል የሚል እምነት የለኝም›› ያሉት የኮቤ ዩኒቨርሲቲ ምሁሩ ፕሮፌሰር ኬንታሮ ኦሊምፒኩ ከመካሄዱ አስቀድሞ በሁለት ጉዳዮች እርግጠኛ መሆን እንደሚያስፈልግ አስቀምጠዋል። አንደኛው የቫይረሱ ስርጭት መገታት ወይም መድሃኒት መገኘቱን ማረጋገጥ ሲሆን በሌላ በኩል በሁሉም ዓመል ሰዎች ከቫይረሱ ነፃ መሆናቸውን ማረጋገጥ ነው። ምክኒያት ብለው ያስቀመጡትም በኦሊምፒክ ውድድሩ ከዓለም ዙሪያ አትሌቶችና የስፖርት አፍቃሪዎች በብዛት የሚታደሙበት መሆኑ ነው። በተቀረው ጊዜ ደግሞ ይህን ማረጋገጥ ከባድ ስለሚሆን ኦሊምፒኩ የመካሄዱ ነገር እውን እንደማይሆን ያስቀምጣሉ። \nበቀጣዩ ዓመት ኦሊምፒኩ ከመካሄዱ አስቀድሞ ጃፓን የቫይረሱን ስርጭት ልትቆጣጠረው እንደምትችል ያላቸውን ተስፋ የገለጹት ፕሮፌሰሩ በተመሳሳይ አንዳንድ አገሮች በተለይም ያደጉ የሚባሉት ቫይረሱን መቆጣጠር ቢችሉ እንኳን ሁሉም የዓለም አገራት በተመሳሳይ ወቅት ሊሳካላቸው እንደማይችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል። ይህ ከግንዛቤ ሲገባም ኦሊምፒኩ በቀጣዩም ዓመት የመሰረዝ ወይም የመራዘም እድሉ ሰፊ መሆኑን አስረድተዋል። \nበዓለም ላይ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ከተስፋ በስተቀር የቫይረሱ ስርጭት በጊዜ የሚገታ ወይም ፈውስና ክትባት በዚህ ጊዜ እውን ይሆናል የሚያስብል እንዳልሆነ መታዘብ ይቻላል። ይህንን ከግምት ያስገቡት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ኦሊምፒኩ የቫይረሱን ስጋት ለማምለጥ በአስራ ስድስት ወራት ቢራዘምም ከቫይረሱ ተፅዕኖ ሊያመልጥ እንደማይችል ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ማመልከታቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ማስነበቡ ይታወሳል።\nአዲስ ዘመን ሚያዝያ 15/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "884909eaf865b92a51440a12e2ab8e6d" }, { "passage": "አንደኛው በደቡም ምሥራቅ አውሮጳ የሚገኙ ቴኒስ ተጫዋቾች ከውድድር ርቀው ስለነበር ለቀጣይ ውድድር እንዲዘጋጁ ለማድረግ ሲሆን ሁለተኛው የሚገኘው ገቢ ከኮሮና ጋር በተያያዘ የሚውል ለበጎ አድራጎት እንዲሰጥ ነበር፡፡\n\nይህ ውድድር ገና ከመጀመሩ ታዲያ አሳዛኝ ዜና አጋጥሞታል፡፡\n\nቢያንስ አራት የሚሆኑ ዕውቅ የቴኒስ ተጫዋቾች በኮሮና መያዛቸው ታውቋል፡፡ ከነዚህም መሐል ክሮሺያዊው ቦርና ኮሪክ እና ሰርቢያዊው ቪክተር ትሮይኪ እንዲሁም ቡልጋሪያዊው ግሪጎር ዲሚትሮቭ ይገኙበታል።\n\n• ኢትዮጵያ መሰረታቸውን ግብጽ ባደረጉ ቡድኖች የመረጃ መረብ ጥቃት ተሞከረብኝ አለች \n\n• የናይጄሪያ ፖሊስ በሩዝ ፋብሪካ ተቆልፎባቸው እንዲሰሩ የተገደዱ 300 ሰራተኞችን ነፃ ማውጣቱን ገለፀ\n\n• በአፍሪካ የመጀመሪያው የኮሮናቫይረስ ክትባት ሙከራ ሊደረግ ነው \n\n‹‹ይህንን የቴኒስ ውድድር ያሰናዳሁት ከቅን ልቦና ተነስቼ ነበር፡፡ ሁሉንም የጤና መመርያዎች ለመከተል ሞክረናል፡፡ ይህ አሳዛኝ ዜና በመምጣቱ ከልብ አዝናለሁ›› ብሏል ቾኮቪች፡፡\n\nየእንግሊዙ እውቅ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች አንዲ ሙሬይ በበኩሉ ‹‹ይህ ለኛ ትልቅ ትምህርት ነው›› ሲል ትዊተር ሰሌዳው ጽፏል፡፡\n\nይህንን ውድድር በዚህ ወቅት ማሰናዳት አደጋ ሊኖረው ይችላል የሚል ሐሳብ ቀድሞውንም ሲንጸባረቅ ነበር፡፡\n\nየቴኒስ ውድድሩ በጆኮቪች ሐሳብ አመንጪነት ሲሰናዳ እውቅ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋቾች ራሳቸውን ከውድድር በማራቃቸው እንደ ማነቃቂያ ሊሆናቸው ይችላል፤ በዚያውም የበጎ አድራጎት ሥራ ይሆናል በሚል ነበር፡፡\n\nጆኮቪች በድረገጹ እንደጻፈው መጀመርያ ቤልግሬድ እንደደረሰ በኮሮና መያዙ ይፋ የተደረገው ኖቫክና ቤተሰቡ ነበር፡፡ ሆኖም ምንም ምልክት አያሳይም ነበር፡፡\n\nይህ በሰርቢያ የተሰናዳው ውድድር 4ሺህ ሰዎች ታድመውታል፡፡ ሜዳ ቴኒስ ተጫዋቾችም ከውድድር በኋላ መሸታ ቤት ሲደንሱ የሚያሳይ ፎቶ ወጥቷል፡፡\n\nበመጀመርያው ቀን ውድድር የቡልጋሪያው ዲሚትሮቭ ከክሮሺያው ኮሪክ ጋር ቅዳሜ እለት ተጫውተው ነበር፡፡\n\nጆኮቪች ከዚህ ቀደም የኮሮናቫይረስ ክትባት ቢኖር እንኳ ክትባቱን ለመወጋት ፍቃደኛ እንደማይሆን በትዊተር ገጹ በመጻፉ የሴራ ንድፈሐሳብ አራማጆች ክትባቱ በቢልጌትስ የተቀነባበረ ስለመሆኑ እንደ አንድ ማስረጃ የርሱን ጽሑፍ ሲያጋሩ ነበር፡፡\n\nሚስቱ ጄሌና ከዚህ ቀደም ኮሮናቫይረስ የመጣው በ5ጂ ቴክኖሎጂ ነው የሚል ይዘት ያለው ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ ማጋራቷ ሲታይ ቤተሰቡ በወረርሽኙ ምንነት ላይ ጥርጣሬ እንደነበረው እንዲገመት በር ከፍቷል።\n\n ", "passage_id": "d4985eb127c590458d9176170cb2a342" }, { "passage": "ቦጋለ አበበበኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ወረርሽኙ መፍትሄ ባያገኝም እንደሚካሄድ እርግጠኛ የሚያደርጉ ማሳያዎችን አዘጋጆቹ ይፋ ሲያደርጉ ሰንብተዋል፡፡ ይሁን እንጂ በውድድሮች ለመሳተፍ ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ አትሌቶችና የስፖርት ቤተሰቦች ከወረርሽኙ ስጋት ጋር በተያያዘ ማሟላት ስለሚጠበቅባቸው መስፈርቶች ወጥ የሆነ ህግ በማውጣት ረገድ አዘጋጆቹ ለረጅም ጊዜ እንደተቸገሩ ይታወቃል፡፡ ይህም የቶኪዮ ኦሊምፒክ የመሰረዝ እድል ይገጥመዋል የሚል ስጋት በብዙዎች ዘንድ አሳድሮ ነበረ፤ይሁንና አዘጋጆቹ ከወረርሽኙ ስጋት ጋር በተያያዘ ተቸግረውበት የነበረውን ህግ ሰሞኑን ይፋ ማድረጋቸው ታውቋል፡፡ ወራትን ከፈጀ ምክክር በኋላ ሃምሳ አራት ገፅ የያዘ ሪፖርት ይፋ ያደረጉት የኦሊምፒኩ አዘጋጆች ወረርሽኙ በቀጣይ ሰባት ወራት ውስጥ መፍትሄ ባያገኝ እንኳን ኦሊምፒኩ መካሄድ የሚችልባቸውን ከጤና ጋር የተያያዙ ሕግና ደንቦች ይፋ አድርገዋል፡፡ በዚህም አትሌቶችም ይሁኑ ተሳታፊዎች መደበኛ የኮቪድ-19 ምርመራ ማድረጋቸው እንደማይቀር ያስቀመጡ ሲሆን፣ ከወረርሽኙ ስጋት ጋር በተያያዘ የሚቀመጡ ገደቦችን የጣሰ ማንኛውም አትሌት የሚቀጣበትን ሕግ እንዳረቀቁ አስታውቀዋል፡፡ ውድድሩን ለመከታተል ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ የስፖርት ቤተሰቦች ለይቶ የማቆያ ጉዳይ እንደሚመለከታቸው የተገለፀ ሲሆን፣ ወረርሽኙን ለመከላከል ከሚያስፈልጉ የጥንቃቄ ርምጃዎች መካከል የአፍ ጭንብል ማጥለቅና አለመጨባበጥን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚገደዱም ተጠቁሟል፡፡ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዝግጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ጥብቅ የመከላከል ርምጃዎች ተግባራዊ እንደሚሆኑ ጠቁመው፣ ይህ የኦሊምፒኩን ድባብ የተለየ ቢያደርገውም በደማቅ ሁኔታ እንደሚከናወን ያላቸውን እምነት ለመገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል፡፡ ከየትኛውም አገር ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ አትሌቶች ጃፓን እንደደረሱ የኮቪድ-19 ምርመራ ይደረግላቸዋል፤ በኦሊምፒክ መንደር በሚኖራቸው ቆይታም በአራት ወይም አምስት ቀናት ልዩነት ተመሳሳይ ምርመራ ይደረግላቸዋል፡፡ በተለያዩ ምርመራዎች ወረርሽኙ የሚገኝባቸውን አትሌቶች በተመለከተም የማገገሚያ ማዕከል እንደሚኖር ተጠቁሟል፡፡ ይሁን እንጂ አትሌቶች በውድድር ወቅት በወረርሽኙ ቢጠቁ የውድድር ሕጎች ላይ ስለሚያሳድረው ተፅዕኖ የተገለፀ ነገር የለም፡፡ አትሌቶች ከውድድርና ልምምድ ውጪ የአፍ መሸፈኛ ጭምብል የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ተጠቁሟል፤ ድምፅን ከፍ አድርጎ ማውራትና ከሌሎች ጋር ንኪኪ መፍጠር እንደማይችሉ ተገልጿል፡፡ ለዚህም እያንዳንዳቸው በቅድሚያ ለነዚህ ሕጎች ተገዢ እንደሆኑ የሚያረጋግጡበት የስነምግባር ደንብ እንደሚፈርሙ ታውቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሁሉም አገራት የስፖርት ልዑካን ቡድኖች ውድድሮቻቸውን እንዳጠናቀቁ በፍጥነት አገሪቱን ለቀው መውጣት እንዳለባቸውና ውድድሮች ከተጠናቀቁ በኋላ ለጉብኝት ወይም ለሽርሽር ተጨማሪ ቀናትን በጃፓን መቆየት እንደማይቻል ተገልጿል፡፡ የተቀመጡትን ሕግና ደንቦች ጥሰው የተገኙ አትሌቶች ወይም የስፖርት ቤተሰቦች ምን አይነት ቅጣት እንደሚጠብቃቸው እስካሁን የተቀመጠ ነገር ባይኖርም አዘጋጆቹ ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጋር በዚህ ጉዳይ ላይ እየሰራ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ የተቀመጡት ደንቦች ስፖርት መዝናኛ እንደመሆኑ በመጠኑም ቢሆን የማስጨነቅ ባህሪ እንዳላቸው ቢታመንም ሕጎቹን እንደ ወንጀል መቅጫ ሕግ መመልከት ሳይሆን ለጥንቃቄ ሲባል የተወሰዱ እንደሆኑ መገንዘብ አስፈላጊ እንደሚሆን አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ ሕግና ደንቦቹን አትሌቶችና ልዑካን ቡድኖች በአግባቡ እንዲገነዘቡ በቡድን መሪዎች በኩል የተለያዩ ማብራሪያዎችና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ይፈጠራሉ፤ስቴድየም ገብተው ውድድሮችን የሚመለከቱ የስፖርት ቤተሰቦችን ቁጥር ለመወሰን ወቅቱ ሲደርስ የወረርሽኙ ስርጭት በዓለም ላይ የሚኖረውን ነባራዊ ሁኔታ መጠበቅ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል፡፡ በኦሊምፒኩ ለመታደም ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ የስፖርት ቤተሰቦች ለሁለት ሳምንታት በለይቶ ማቆያ እንዲቀመጡ ማድረግ እንደማይቻል የገለፁት አዘጋጆቹ፣ ሌሎች አማራጮችን እንደሚጠቀሙ ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ የወረርሽኙ ክትባት እንደተገኘና በርካታ አገራትም በግዢ ሂደት ላይ እየተረባረቡ መሆኑ እየተሰማ ቢሆንም፣ ኦሊምፒኩ እስከሚካሄድበት ወቅት ድረስ ለዓለም ሕዝብ ሊዳረስ ስለማይችል የኦሊምፒኩ አዘጋጆች አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ ውድድሩን በታሰበው ጊዜ ማካሄድ የግድ እንደሆነ አምነው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ የወረርሽኙን ስጋት ለመቅረፍ በሚደረጉ የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎች የኦሊምፒክ አዘጋጆች ምን ያህል ወጪ እንደሚጠብቃቸው ቁርጥ ያለ መረጃ ባይኖርም፣ ባለፈው ሳምንት የወጡ ሪፖርቶች እስከ አንድ ቢሊየን ዶላር ሊፈጅ እንደሚችል አመላክተዋል፡፡ ኦሊምፒኩን በታቀደው ጊዜ ማካሄድ ካልተቻለና የመራዘም እድል ከገጠመው ደግሞ አዘጋጆቹ ቀደም ብለው ከያዙት በጀት እስከ ሁለት ቢሊየን ዶላር ድረስ ተጨማሪ ወጪ ሊያወጡ እንደሚችሉ በቅርብ የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 30/2013", "passage_id": "59e014c49aaf9951044da734cee2ec85" }, { "passage": "የዓለምን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ወደተለየ አቅጣጫ ያዞረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በስፖርቱ ዓለም ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተዘርዝሮ የሚልቅ አይደለም። አንዳች ውድድር በዓለም ላይ እንዳይኖር ከማስገደድ ባለፈ የስፖርቱን ዓለም ሽባ አድርጎታል። ብዙ ታቅዶባቸው፣ብዙም ተለፍቶባቸው ለዓመታት በዝግጅት ላይ የነበሩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በትልቅ ኪሳራ የሚካሄዱበት ጊዜ እንዲራዘም ግድ ብላል። \nየኮሮና ቫይረስ ስርጭት በዓለም ዙሪያ ከተንሰራፋ ወዲህ በግለሰብ ደረጃ ካልሆነ በስተቀር የትኛውም የስፖርት እንቅስቃሴ ተገድቦ እንደቆየ ይታወቃል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ይመለሳሉ የሚል ተስፋ የለም። ይሁን እንጂ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሐግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር እንደሚመለሱ ተስፋ መስጠታቸው አልቀረም። የዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን ለግሰዋል። \nበዓለማችን ብሎም በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ስርጭትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የስፖርት ቤተሰቡ መደበኛ እንቅስቃሴውን ገቶ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ ከጀመረ ሰነባብቷ። የስፖርት ቤተሰቡ ወረርሽኙን ለመከላከል ግንዛቤ ከመፍጠር እስከ ደም ልገሳ፤ ከቁሳቁስ እስከ ገንዘብ ድጋፍ በማድረግ አጋርነቱን አሳይቷል ፤ በማሳየት ላይም ይገኛል። \nወረርሽኙ በዓለም ላይ ከተከሰተና ከተስፋፋ ወዲህ የስፖርቱን ዘርፍ ክፉኛ የጎዳው ሲሆን የአገራችንን ጨምሮ በዓለም ላይ በርካታ ታላላቅ ውድድሮች እንዲቆሙ አስገድዷቸዋል። በተለይም ወረርሽኙን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በተወሰዱ እርምጃዎች ስልጠናዎች፣ ውድድሮች ቁመዋል ፤ ስፖርተኛው እና የስፖርት ቤተሰቡ ከፍተኛ የሆነ የስነ ልቦና እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አጋጥሟቸዋል ። \nበርካታ የስፖርት ክለቦች የመፍረስ አዳጋ ተደቅኖባ ቸዋል፤ አንዳንዶቹም ለስፖርተኞች ወርሃዊ ደመወዝ እስከ መከልከል ደርሰዋል። በመሆኑም የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በወረርሽኙ ወቅት እና ከወረርሽኙ በኋላ ስፖርቱ እንዴት ወደ ነበረበት መመለስ ያስችላል የሚለውን የሚያጠና እና ለመንግሥት የሚያቀርብ ጠንካራ ኮሚቴ መቋቋሙን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጅሎ መናገራቸውን የተቋሙ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ ላይ ተዘግቧል። \nየተቋቋመው ኮሚቴ አብይ እና ቴክኒካል ኮሚቴ ያለው ሲሆን አብይ ኮሚቴው በባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ጣሰው የሚመራ ይሆና። ቴክኒካል ኮሚቴው ደግሞ በአቶ ዱቤ ጅሎ እንደሚመራ ታውቋል። \nኮሚቴው አጠቃላይ የኮሮና ወረርሽኝ በአገራችን ስፖርት ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና እና መፍትሔዎችን በማጥናት ሰነዱን ለመንግሥት የሚያቀርብ ይሆናል። በጥናቱም የሌሎች አገራት ተሞክሮ ምን እንደሚመስል ተካቶ እንደሚቀርብ አቶ ዱቤ አብራርተዋል። \nጥናቱን መሠረት በማድረግ መንግሥት ስፖርቱ ለአገራችን ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ ግምት ውስጥ በማስገባት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምክትል ኮሚሽነሩ ገልፀዋል ።አዲስ ዘመን ግንቦት 27/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "24c212eb0cbc2bfc4fa9a396312bd847" } ]
01bbbf1b016028279ffc7126fd76bc19
763e69a1ce3e1e4de76f19ef0274486d
በደቡብ ክልል በተፈጠሩ የጸጥታ ችግሮች ተሳትፎ ያደረጉ 711 አመራሮች ከኃላፊነት ተነሱ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በደቡብ ክልል ከዚህ ቀደም በተፈጠሩ የጸጥታ ችግሮች ተሳትፎ ያደረጉ 711 አመራሮች ከኃላፊነት መነሳታቸውን የደቡብ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሰናይት ሰለሞን አስታወቁ። ኃላፊዋ በክልሉ የተካሄደውን የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት አፈጻጸም ግምገማ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።በመግለጫው ወቅትም፣ በክልሉ በጉራፈርዳ፣ በወላይታ፣ በኮንሶ ዞን እና በዙሪያው ባሉ ልዩ ወረዳዎች የአደረጃጀት እና የወሰን ጥያቄዎችን መነሻ በማድረግ የሕዝቡን ጥያቄዎች በኃይል ማስፈጸም ይቻላል በማለት የህወሓት ጁንታ ለግጭት አመቺ የሆኑ ቦታዎችን በመጠቀም ህብረተሰቡ ያልተገባ ዋጋ እንዲከፍል ማድረጉን ተናግረዋል።በብዝሀነቱ የሚታወቅና ለሌሎች አካባቢዎችም ተምሳሌት የሆነውን የደቡብ ክልል ጽንፈኛው የህወሓት ጁንታ ኃይል ለእኩይ አላማ ሲጠቀምበት እንደነበርም በዝርዝር መገምገሙን የገለጹት ወይዘሮ ሰናይት፤ ጽንፈኛው ቡድን ኢ-መደበኛ አደረጃጀቶችንበመጠቀም ሀብት በመመደብ ሲንቀሳቀስ መቆየቱንም አብራርተዋል።በዚህ ምክንያት በተፈጠረው ችግር በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጃቸው መኖሩ የተረጋገጠ 711 አመራሮች ከኃላፊነት መነሳታቸውን በመጠቆምም፤ 918 የሚሆኑት ደግሞ ከቦታቸው እንዲሸጋሸጉ መደረጉን ተናግረዋል። በተጨማሪም 1 ሺህ 966 አመራሮች በማስጠንቀቂያ መታለፋቸውን መግለጻቸውን ነው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት የክልሉን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ጠቅሶ የዘገበው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37996
[ { "passage": "የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት በመተከል ዞን ከተፈጠረው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ እጃቸው አለበት የተባሉ ከፍተኛ እና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችን በህግ ቁጥጥር ሥር ማዋል ጀምሯል፡፡በዞኑ በተፈጠረው የጸጥታ ችግር እጃቸው ያለበትን፣ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ አመራሮችን በህግ ቁጥጥር ስር እያዋለ ሲሆን እስካሁንም 5 አመራሮችን በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡በዚህም መሠረት፡-1ኛ. አቶ ቶማስ ኩዊ፡- የኢፌዴሪ ሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማኅበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ2ኛ. አቶ አድጎ አምሳያ፡- የቀድሞው የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር3ኛ. አቶ ሽፈራው ጨሊቦ፡-የቀድሞ የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር4ኛ. አቶ ባንዲንግ ማራ፡- የመተከል ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ5ኛ. አረጋ ባልቢድ፡- የመተከል ዞን የቀድሞ አመራር የነበሩእነዚህ አመራሮች ከመተከል ዞን የጸጥታ ችግር ጋር እጃቸው እንዳለበት በመረጋገጡ በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡የክልሉ መንግስት በዞኑ የተፈጠረውን ግጭት ለማረጋጋት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ሲሆን፣ ከተፈጠረው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ተሳትፎ ባደረጉ በየደረጃው በሚገኙ አመራሮች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡በመሆኑም ህብረተሰቡ የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር ወደ ሠላም ለመመለስ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ እንዲደግፍ የክልሉ መንግስት ጥሪ ማቅረቡን ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡", "passage_id": "338b8696a02d3e4649394978f30bfe38" }, { "passage": "የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) ድርጅታዊ ጉባዔ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፣ ሽፈራው ሽጉጤን እና ሲራጅ ፈጌሳን ጨምሮ 23 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላቱን በክብር አሰናበተ።ደኢህዴን በሀዋሳ ከተማ እያካሄደ ባለው ጉባዔ ነው ነባር አመራሮቹን በክብር ያሰናበተው።በዚህም መሰረት፦1. አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ2.አቶ ሽፈራው ሽጉጤ3. አቶ ሲራጅ ፈጌሳ4. አምባሳደር ተሾመ ቶጋ5. አቶ ተክለወለድ አጥናፉ6. አቶ ሳኒ ረዲ7. አቶ ታገሰ ጫፎ8. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን9. ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም10. አቶ ደበበ አበራ11. አቶ መኩሪያ ሀይሌ12. አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ13. አቶ ካይዳኪ ገዛኸኝ14. አቶ ተመስገን ጥላሁን15. አቶ ወዶ ኦጦ16. አቶ ያዕቆብ ያላ17. አቶ ሰለሞን ተስፋዬ18. አቶ ፀጋዬ ማሞ19. አቶ ንጋቱ ዳንሳ20. አቶ አድማስ አንጎ21. አቶ ኑረዲን ሀሰን22. አቶ ሞሎካ ወንድሙ23. አቶ አብቶ አልቶ ናቸው ከማእከላዊ ኮሚቴው በክብር የተሰናበቱት።ከማእከላዊ ኮሚቴ የተሰናበቱት አባላት ከ15 እስክ 17 ዓመታት በተለያየ የሀላፊነት ደረጃ ያገለገሉ መሆናቸውም ተገልጿል።ጉባዔው በተጨማሪም ከድርጅቱ ኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን አቶ ካሚል አህመድን በክብር አሰናብቷል።እንዲሁም እስከ 10ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ በእግድ እንዲቆዩ አድርጓቸው የነበሩ አባላትንም አሰናብቷል።በዚህም መሰረት፦1. ወይዘሮ አማረች ኤርሚያስ2. አቶ ሳሙኤል ደምሴ3. ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ ከድርጅቱ ተሰናብተዋ  ", "passage_id": "a1c58ccc9c664e434addd5ee315185f2" }, { "passage": "ጋምቤላ ፤ ህዳር 25/2006 (ዋኢማ) – በጋምቤላ ክልልና በፌደራል ልዩ ደጋፍ ቦርድ እየተከናወኑ ያሉት የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለፀ።በፌደራል ልዩ ድጋፍ ቦርድ ስብሳቢ አቶ አዲሱ ለገሰ የሚመራው የግብርና፣ የትምህርት ፣ የፌደራል ጉዳይ ሚኒስተሮችና ሚኒስተር ዴኤታዎች ቡድን፣ እንዲሁም የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት የ1ኛው ሩብ በጀት ዓመት የጋራ ስራ አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል።በጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አዳራሽ ለሁለት ቀናት በተካሄደው ግምገማ ላይ በተለይም በመንደር ማሰባሰቡ ተጠቃሚ የሆኑት ከ37 ሺህ በላይ የቤተሰብ መሪዎችን የመሰረተ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት የሚያበረታታ መሆኑን አቶ አዲሱ ገልፀዋል።የፌደራል ጉዳዮች ሚኒሰትር ዴዔታ አቶ ሙሉጌታ ውለታው በበኩላቸው በትምህርት፣ በጤና፣ በወፍጮና በንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ዘርፍ የሚታዩ ክፍተቶች በአፋጣኝ ሊቀረፉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጋትልዋክ ቱትና ምክትላቸው ኢንጂነር ኡሌሮ ኦፒየው በበኩላቸው እንደገለጹት የክልሉን ህዝብ ኑሮ ለማሻሻልና አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል።በጋራ የምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ከውይይታቸው በፊት በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው መጎብኘታቸውን የዋልታ ኢንፎርሜሽን ዘገባ ያመለክታል።", "passage_id": "1e303374076dc0ea7c27ceca5bae9a3d" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ ክልል በሸካ እና ቤንች ሸኮ ዞኖች የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር ለመቅረፍ  እየተሰራ መሆኑን የክልሉ የፀጥታ እና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።ቢሮው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጸው፥ ባለፉት 2 ሳምንታት ቴፒ ከተማን ጨምሮ በተፈጠረው ግጭት የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል።ግጭቱ በአካባቢው የመዋቅር አደረጃጀት ጥያቄን ወደ ግጭት ለመውሰድ በሞከሩ የተደራጁ ቡድኖች የተፈጠረ ስለመሆኑም ገልጿል።ከአንድ አመት ወዲህ በአካባቢው ተደጋጋሚ ግጭቶች ሲከሰቱ ይስተዋላል።የክልሉ ፀጥታ በኮማንድ ፖስት ስር እንዲጠበቅ ከመደረጉ አስቀድሞም ይህን ግጭት ለማርገብ ያለመ የፀጥታ ሀይል ቁጥጥር መጋቢት 20 ቀን 2011 ዓ.ም ስራ መጀመሩም ይታወሳል።ሆኖም የተረጋጋ እየመሰለ አልፎ አልፎ በሚከሰት ግጭት የአካባቢው ፀጥታ ታውኳል።የደቡብ ክልል የጸጥታና አስተዳደር ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በስልክ በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፥ በሸካ ዞን እና በቤንች ሸኮ ዞን የሚከሰተው አለመረጋጋት ምክንያቱ የመዋቅር ጥያቄ ነው።ይሁን እንጅ ከውይይት ይልቅ ግጭትን በመረጡ የተደራጁ ቡድኖች ችግሩ መፈጠሩንም አውስተዋል።በሁለቱ ዞኖች በተለይም ከሸካ ዞን ቴፒ ከተማ እና በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ዳግም የፀጥታ ችግሩ ማገርሸቱን ገልጸዋል።የህዝቡን ጥያቄ ለግጭት መንስኤ ያደረጉ ሀይሎች መንገድ መዝጋት እና የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን እንዲዘጉ የማስገደድ ተግባር ፈጽመዋልም ነው የሚሉት።የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ ሀይልም አካባቢውን ለማረጋጋት እየሰሩ መሆኑንም አንስተዋል።በዚህ የፀጥታ ችግር ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋምና በወንጀል የተጠረጠሩ አካላትን ለመያዝ በተደረገ ጥረት የፀጥታ ሀይል አባልን ጨምሮ 7 ሰዎች መሞታቸውን ተናግረዋል።ምክትል የቢሮ ሀላፊው ትክክለኛውን የህዝቡን የመዋቅር አደረጃጀት ጥያቄ በውይይት ለመፍታት የክልሉ መንግስት እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፥ ሆን ብለው አካባቢው እንዳይረጋጋ የሚሰሩ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል ብለዋል።እስካሁን 68 ተጠርጣሪዎች ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት በማድረግ በወንጀል የተጠረጠሩትን በህግ ፣ እርቅ የፈጸሙትን ደግሞ ወደ ህብረተሰቡ የመቀላቀል ስራ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።በቴፒ ከተማ ከትናንት ጀምሮ አንጻራዊ ሰላም እየታየ ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ሃላፊው፥ ዞኖቹን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ለመመለስ ከህዝቡ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።አስተያየታቸውን ለጣቢያችን የሰጡ የቴፒ ከተማ ነዋሪዎች ባለፉት ሁለት ቀናት አንጻራዊ ሰላም በከተማዋ እየታየ መሆኑን ነግረውናል።መንግስትም በዘላቂነት ህግ እና ስርዓትን በማስከበር ለመዋቅር ጥያቄው ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጢሞቲዎስ ሙሉጌታ በኩላቸው፥ ከፀጥታ ችግሩ ጋር ግንኙነት ያላቸውን አካላት በህግ ጥላ ስር ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።ከተማዋን በተሻለ ለማረጋጋትም ከህዝቡ ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በሀይለእየሱስ መኮንንትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!\nhttps://t.me/fanatelevision", "passage_id": "62564ecc434f98418374f3a32b5c72ea" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 18 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮንሶ እና በአሌ አከባቢ ተፈጥሮ የነበረውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት ውይይት ተካሄደ፡፡በውይይቱ የኮንሶ እና የአሌ ህዝቦች ለረጅም ዘመናት የዘለቀ አብሮነታቸውን በማስቀጠል እርስ በርስ እንደ አንድ የቤተሰብ አባል ሆነው መዝለቃቸው ተነስቷል፡፡ይህ አንድነታቸው ያላስደሰታቸው አካላት ግን የግል ጥቅም እና ፍላጎታቸውን መሠረት በማድረግ የጸጥታ ችግር እንዲከሰት ምክንያት ሆነዋል ነው የተባለው፡፡ዛሬ ግን የኮንሶ እና የአሌ ህዝቦች የቀደመ ሠላማቸውን ለማስቀጠል በየአካባቢያቸው  ያለውን የመተሳሰብ እና የመደጋገፍ ባህል ለማስቀጠል ውይይት በማካሄድ ላይ ናቸው፡፡በመድረኩ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳው፣ የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጥላሁን ከበደን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል፡፡አቶ እርስቱ ይርዳው ህብረተሰቡን እርስ በእርስ በማጋጨት እና መሳሪያ በመሸጥ ሀብት ከሚያጋብሱ አካላት እራሱን መጠበቅ ይኖርበታል ብለዋል፡፡የኮንሶና የኧሌ ህዝቦች እርቀ ሰላም በማስፈናቸው የተሰማቸውን ልባዊ ደስታ በእርሳቸው እና በክልሉ ህዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ይህ እርቀ ሰላም ኮንፈረንስ በኮንሶና በደራሼ ህዝቦችም መካከል ሊካሄድ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡እንዲህ አይነቱ የሰላም ጥሪ በሌሎች አካባቢዎችም ፈጥኖ ሊተገበር እንደሚገባ ጠይቀዋል፡፡አሁን የተጀመረው ሰላም እንዲሰፍን የክልሉ መንግሥት በትኩረት ሲሰራ እንደነበርም አብራርተዋል፡፡የኮንሶና የኧሌ ሽማግሌዎች እና አመራሮች ያከናወኑት አኩሪ ተግባር በሌሎች  የክልሉ አካባቢዎችም እንዲደገም ጥሪ አቅርበዋል፡፡በደቡብ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የኮንሶና የኧሌ ህዝቦች አንድ ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል፡፡ተሸናፊው የህወሀት ቡድን አጀንዳ አስፈጻሚዎች በፈጠሩት ችግር የአካባቢው ሰላም እንዲደፈርስ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡በተፈጠረው ችግር እጃቸው አለበት ተብሎ የተጠረጠሩ 310 ሰዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አቶ አለማየሁ ገልጸዋል፡፡በሁለቱም ወገን ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን ወደ ህግ የማቅረብ ስራ ይሰራልም ብለዋል፡፡በጸጥታ ችግር የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ በትኩረት እንደሚሰራ አብራርተዋል፡፡በሰላም ኮንፈረንሱ የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኩታዬ ኩሲያ እና የኧሌ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማታማ ማጋ እንደገለጹት ከዚህ ቀደም ጠንካራ ትስስር ያላቸው ህዝቦች መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ሁለቱ ህዝቦች መካከል ችግር ቢፈጠር እንኳ ለችግሮች መፍትሄ የሚሰጡበት ባህላዊ ዳኝነት እንዳላቸው ጠቅሰው የጎሳ መሪዎች እንደ አንድ የቤተሰብ አባል ለሚፈጠሩ አለመግባባቶች መፍትሄ ሲሰጡ ቆይተዋል ብለዋል፡፡ዋና አስተዳዳሪዎቹ በንግግራቸው እንደገለጹት የቀጠናውን ሰላም የማይፈልጉ ሀይሎች በፈጠሩት እኩይ አጀንዳ የሁለቱን ህዝቦች ዋጋ  ያስከፈለ ድርጊት ተፈጽሟል፡፡ከዚህ ቀደም የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር በዘላቂነት በመፍታት የኮንሶ እና የኧሌ ህዝቦች የቀደመ ቤተሰባዊ ትስስራቸው እንዲቀጥል የሰላም ኮንፈረንሱ ፋይዳው የጎላ እንዲሆን ያደርገዋልም ብለዋል፡፡ችግሩ እንዲፈጠር ተዋናይ የነበሩ ሰዎችን በህግ እዲጠየቁ ይደረጋል ሲሉ ነው ዋና አስተዳዳሪዎቹ በንግግራቸው መጠቆማቸውን ከደቡብ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል www.youtube.com/fanatelevision ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!", "passage_id": "cf8558ebd09d6d4af9aa92de2e545ab9" } ]
d52d0a34a16f53fb4256930824745cd0
759a58c777b87995516473b2befd836b
ፎረሙ፣ የሕንድ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሰማሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ
በኃይሉ አበራአዲስ አበባ፡- የሕንድ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ባሉ ሰፊ የኢንቨስትመንት ዘርፍ አማራጮች እንዲሰማሩ የማማከርና የግንዛቤ ድጋፍና እንደሚያደርግ በኢትዮጵያ የሕንድ ኢንቨስተሮች ፎረም አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከትናንት በስቲያ በተሻሻለው የኢንቨስትመንት ሕግ ዙሪያ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የሕንድ ባለሃብቶች ገለጻ አድርጓል።በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ የሕንድ ኢንቨስተሮች ፎረም ሊቀመንበር ማዮር ኮታሪ እንደገለጹት፤ ፎረሙ የህንድ ባለሀብቶችን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችል ነው። ኢትዮጵያ ያፀደቀችው አዲሱ የኢንቨስትመንት ዓዋጅ ደግሞ በተለይ ለውጭ ባለሃብቶች ዝግ የነበሩ ዘርፎችን ክፍት በማድረጉ ባለሀብቶችን ያበረታታል። በመሆኑም የሕንድ ባለሃብቶች ይሄን እድል ተጠቅመው በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሰማሩ ፎረሙ ድጋፍ ያደርጋል።የሕንድ ባለሀብቶችና በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በእርሻ፣ በቱሪዝም፣ በትምህርትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በኬሚካል፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ በመድኃኒት መስኮች ተሰማርተው እየሰሩ መሆኑን ያስታወቁት ሊቀመንበሩ፤ ፎረሙ ከሕንድ የሚመጡ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ጥረት እንደሚያደርግም ገልጸዋል። እንደ ሊቀመንበሩ ገለጻ፤ የህንድ ቢዝነስ ፎረም ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የማበረታታት እና የማማከር ስራ እየሰራ ይገኛል። ከውጭ ሀገር የሚመጡ ኢንቨስተሮች ወደ ኤምባሲ ሲሄዱ ኤምባሲው የህንድ ኢንቨስትመንት ፎረም የማማከር አገልግሎት እንዲያገኙ የሚልክበት የትስስር አሰራርም አለው። በመሆኑም በፎረሙ አማካኝነት ያሉትን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ከፎረሙ ጋር በመወያየት አዋጭ በሆነው የኢንቨስትመንት ውሳኔ ላይ ይደርሳሉ።የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እያዘጋጀ በሚገኘው ዓይነት ሴሚናሮችም ከመንግስት አካላት ጋር ውይይት የሚያስፈልግ ከሆነ በኤምባሲው በኩል የምክክር መድረክ በማዘጋጀት ፎረሙ የበኩሉን እገዛ እንደሚያደርግ የገለጹት ሊቀመንበሩ፤ ይሄን አይነት አሰራር መኖሩ ደግሞ በርካታ ችግሮችን ተወያይቶ ለመፍታትም ሆነ በውጭ ያሉ ባለሃብቶች ግንዛቤ ፈጥረው ወደኢትዮጵያ እንዲመጡ እድል የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል።ከህንድ የሚገቡ ቴክኖሎጂዎች በተመጣጣኝ ዋጋ የሚቀርቡ በመሆናቸው እና ባለሙያዎችም ጭምር አብረው የሚገቡ በመሆኑ ለቴክኖሎጂ ሽግግሩም ሆነ በኢትዮጵያ ካለው የኢኮኖሚ አቅም አኳያ በቀላሉ የሚለመዱ በመሆኑ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸው መሆኑን በመግለጽም፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ኢንጂነሮች እና ቴክኒሽያኖች ከህንድ ከመጡት ባለሙያዎች ልምድ እየወሰዱ በመሆኑ በተለያዩ ፋብሪካዎች የሚበረታታ የቴክኖሎጂ ሽግግር እየተስተዋለ መሆኑንም አመልክተዋል። “ኢትዮጵያ ገና በጣም የሚሰራባት አገር ነች፤ ለመስራትም ብዙ እድሎች ስላሉ የሚመጣው ኢንቨስተርንም ብዙ አማራጮችን መኖሩን እየተመለከተ ነው” ያሉት ሊቀመንበሩ፤ በማዕድን፣ በፋርማሲ፣ አግሮ ኢንዱስትሪ፣ በኬሚካል፣ በቴክኖሎጂ፣ በሶፍትዌር ማበልጸግ እና ሌሎችም ዘርፎች ላይ ያሉ የኢንቨስትመንት እድሎች መጠቀም እንደሚገባም ጠቁመዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37995
[ { "passage": "አዲስ አበባ፤- በኢትዮጵያ የካናዳ ኤምባሲና በኢትዮጵያ የንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በጋራ የኢትዮ-ካናዳ የቢዝነስ ፎረም ሲካሄድ እንደተገለጸው÷ በኢትዮጵያና በአካባቢዋ በሚገኙ አገራት ያለው ከፍተኛ ገበያ የካናዳ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ በተለያየ ዘርፍ እንዲሳተፉ እንደሚያደርጋቸው ተገለጸ። በኢትዮጵያ የካናዳ ኤምባሲ ከፍተኛ የንግድ ኮሚሸነር ሚስተር ሉዊ ላካስ እንደገለጹት÷ በኢትዮጵያና በአካባቢዋ ከፍተኛ የገበያ ዕድል አለ። ይህ ገበያ የካናዳም ሆነ የሌሎች ሀገሮች ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚስብ ነው። የካናዳ ኢንቨስተሮችም በኢትዮጵያ ያለው ገበያ ስቧቸዋል። የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትርና ሌሎች ከፍ ተኛ ባለስልጣናት የንግድ ማህበረሰቡን ወደ ኢትዮጵያ ይዘው የመጡት በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት አማራጭ ለመመልከትና ስምምነት በማድረግ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል። “ከአፍሪካ አገራት ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ምርጫችን በማድረግ በኢትዮጵያና በአካባቢዋ ያለውን ገበያ መጠቀም እንፈልጋለን ያሉት ሚስተር ሉዊ ላካስ በኢትዮጵያ ያለው ባለ ሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ መንግስት እያካሄደ ያለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ እንዲሁም በቀጣይ የሚካሄደው ምርጫ አገሪቱን ጠንካራ የሚያደርግና ለኢንቨስተሮችም ምቹ በመሆኑ የካናዳ ባለሃብቶች ከኢትዮጵያ ጋር በኢኮኖሚው ዘርፍ የሚፈጥሩት ግንኙነት ትልቅ ውጤት የሚያመጣ መሆኑንም ገልጸዋል። የካናዳ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በማዕድን፣ በትራንስፖርት፣ በሆቴል፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖ ሎጂ፣ በገበያ፣ በኢንዱስትሪና በሌሎች ዘርፎች የመ ሰማራት ፍላጎት አላቸው። የካናዳ ኢንቨስተሮች በአፍሪካ ኢንቨስት ሲያደርጉ አዲስ ልምድ በመሆኑ ችግሮች ቢኖሩም ችግሮቹ አንድ በአንድ በመፍታት ውጤታማ እንሆናለን። ኢንቨስተሮቹም በቀጣይ ዓመታት እየበዙ እንደሚሄዱ እምነታቸው መሆኑን የንግድ ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።በኢትዮጵያ ስላለው ነባራዊ ሁኔታና በቀጣይ መንግስት ለመከተል ስላቀደው አገር በቀል የኢኮኖሚ እቅድ ለባለሃብቶቹ ከፕላን ኮሚሽን ማብራሪያ የሰጡት ዶክተር ሰዒድ ኑሩ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በሁለት አሐዝ የኢኮኖሚ ዕድገት ብታስመዘግብም የገቢና ወጭ ንግድ አለመጣጣም፣ የተቋማት የማስፈጸም አቅምና ሙስና የኢኮኖሚው ቀጣይ ዕድገት ላይ ቀጣይ መሆን አለመቻሉም አመላክተዋል። መንግስትም አገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይ ለማድረግ አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አድርጓል። በማሻሻያው የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ፣ ማይክሮ ኢኮኖሚክ ማሻሻያና ተቋማዊ የአሰራር ማሻሻያ አድርጓል። የቴሌኮም፣ የአየር መንገድ፣ በኃይልና በሌሎች ዘርፎችም የግሉ ዘርፍ እንዲገባ መንግስት እየሰራ መሆኑና ለግል አልሚዎች ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል። በግል የመንግስት አጋርነት ዘርፍም የግል ኢንቨስተሮች እንዲሳተፉ ለማድረግም የተለያዩ ጥናቶች እየተካሄዱና ለጨረታም እየወጡ መሆኑም ተገልጿል።የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ እና ልዑካን ቡድናቸውን ትናንት ማለዳ በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው፣ ካናዳ በአያሌ መስኮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ እንደ ሆነች ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የሚካሄዱትን ለውጦች እና ሪፎርሞች እንደሚያደንቁና እንደ ወዳጅ፣ ደግሞም እንደ አጋር በጎን ሆነው ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉም አውስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም በዲሞክራታይዜሽን እና ሁለተናዊ ብልጽግናን በመገንባት ላይ ስለተመሠረቱት ባለብዙ ገጽታ ቀጣይ የሪፎርም ሥራዎች ገልጸዋል።ሁለቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮች የጋራ ፍላጎት በሚስተዋልባቸው የልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ንግድ፣ የኢነርጂ ኢንቨስትመንት፣ አግሮ-ፕሮሰሲንግ፣ መድኃኒት እና ተያያዥ ግብአቶች ላይ በጋራ ስለመሥራት ተወያይተዋል። የቀጣናው ሰላምና ደህንነት ላይ በጋራ መሥራትንም አንዱ የትብብር አቅጣጫ አድርገው አንስተዋል።አዲስ ዘመን የካቲት 1/2012አጎናፍር ገዛኸኝ", "passage_id": "f9fb3f60d8ee6457122bfd49621c72a6" }, { "passage": "ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በቻይና ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ብሔራዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሳን ሩዢ ከሚመራው የቻይና ባለሃብቶች ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡በውውይቱ ወቅትም ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ፥ በኢትዮጵያ ለጨርቃ ጨርቅ አልባሳት ዘርፍ መንግሥት የሚሰጣቸውን ድጋፎች ምቹ ሁኔታዎች በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።የቻይና ባለሀብቶችም በበኩላቸው በኢትዮጵያ ያለው ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታና እምቅ አቅም በዘርፉ ለመሰማራት እንዳነሳሳቸው ገልጸው፣ የፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ማብራሪያም እንዳስደሰታቸውና በቀጣይም በኢትዮጵያ መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ባለሐብቶቹ የሐዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክን ጎብኝተዋል፡፡የቻይና ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ብሔራዊ ምክር ቤት በቻይና ጨርቃ ጨርቅና ተያያዥ ኢንዱስትሪ ዘርፎች የተሰማሩ ከ3 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞችና የጨርቃ ጨርቅ ማህበራትን ያቀፈ ነው።  ", "passage_id": "fbccac514f5a7f547abe56faf4f0f983" }, { "passage": "ኢትዮጵያ በቆዳ ውጤቶች፣ በሲሚንቶ፣ በህንጻ መስታወት ማምረትና በሌሎች የግንባታ ዘርፎች ለሚሰማሩ የቼክ ሪፐብሊክ ባለሃብቶች ጥሩ የገበያ አማራጭ መሆኗን ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ ገለፁ።ፕሬዚዳንቱ ከቼክ ሪፐብሊክ የግብርና ሚኒስትር ጋር የሁለቱን አገራት ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ማጠናከር በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው መክረዋል።ውይይቱን የተከታተሉት የፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት የኮሙኒኬሽን ዳሬክተር አቶ አሸብር ጌትነት እንዳሉት አገራቱ በመሰረተ ልማት፣ በግብርና፣ በግንባታ ዘርፎች፣ በመከላከያና ሌሎች ጉዳዮች በጋራ ለመስራት መክረዋል።   ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸው እኤአ ከ 1947 የተጀመረ ቢሆንም ኢኮኖሚያዊ ትብብራቸው ዳብሮ የአገራቱን ህዝቦች ተጠቃሚ ከማድረግ አንጻር ብዙ እንደሚቀረው በውይይታቸው አንስተዋል።  በመሆኑም ግንኙነታቸው በሚጠናከርበትና የቼክ ሪፐብሊክ መንግስትና ባለሃብቶች ድጋፍ ሊያደርጉባቸው በሚችሉባቸው መስኮች በስፋት ተነጋግረዋል።በቆዳ፣ ሲሚንቶና የህንጻ መስታወት ማምረቻ ዘርፎች ከፍተኛ ልምድና ብቃት ያላቸው የቼክ ሪፐብሊክ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ቢሰሩ የበለጠ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ፕሬዚዳንት ሙላቱ አስረድተዋል።በስፋት እየተካሄደና በርካታ የውጭ ባለሃብቶችን እያሳተፈ ያለው የኢትዮጵያ የግንባታ ዘርፍ ለቼክ ሪፐብሊክ ባለሃብቶች ሰፊ የገበያ አማራጭ መሆን እንደሚችልም አክለዋል።በዘርፎቹ ለሚሰማሩ የአገሪቱ ባለሃብቶች የኢትዮጵያ መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።በኢትዮጵያ ያለውን የገበያ አማራጭ ለአገራቸው ባለሃብቶች በማስረዳት ወደዚህ መጥተው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያወጡ ጥረት እንደሚያደርጉ የገለጹት ደግሞ የቼክ ሪፐብሊክ የግብርና ሚኒስትር ማሪዓን ጁረካ ናቸው።መንግስታቸው ለኩባንያዎቹ የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ጭምር ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንዲሰሩ ሁኔታዎችን እንደሚያመቻች ተናግረዋል።ከፕሬዚዳንቱ ጋር ስለ አገራቱ የቆየ ግንኙነት፣ በኢትዮጵያ እየተተገበሩ ስለሚገኙ ፕሮጀክቶችና የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሁም አገሪቱ በሠላምና ፀጥታ ጉዳይ ባላት የነቃ ተሳትፎ ዙሪያ በሰፊው መወያየታቸውን ገልፀዋል።የቼክ ሪፐብሊክ ባለሃብቶች ከኢትዮጵያ የቢዝነስ አጋሮች ጋር በመሰረተ ልማትና በግብርና መስኮች በጋራ መስራት እንደሚችሉ ነው የተናገሩት።( ኢዜአ)", "passage_id": "cfe1584ea44ab32a61d343716bb0a95f" }, { "passage": "የኦማን የተለያዩ ኩባንያዎች ምርት ኤግዚቢሽን (ኦፔክስ 2016) በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሚያዝያ 3 እስከ 6 (አፕሪል 11-14) በሚሌኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ በኦማን ንግድና ኢንዱስትሪ ሚ/ር፣ በኦማን ንግድ ም/ቤት፣ ፐብሊክ ኢስታብልሽመንት ፎር ኢንዱስትሪያል ኢስቴት፣ ዘ ፐብሊክ ኦቶሪቲ ፎር ኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን ኤንድ ኤክስፖርት ዴቨሎፕመንት የተቋቋመው ኮሚቴ፤ ከአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ም/ቤት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ኤግዚቢሽን በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ከ100 በላይ ኢንዱስትሪዎች እንደሚሳተፉ ታውቋል። ኮሚቴው ባለፈው ረቡዕ በሳሮማያ ሆቴል በሰጠው መግለጫ፣ በተፈጥሮ ማዕድናት፣ በብረታ ብረት፣ በእንጨትና የእንጨት ውጤቶች፣ በፈርኒቸር፣ በምግቦች፣ በሕክምናና በፋርማሲቲካል ምርቶች፣ በማዳበሪያ፣ በፕላስቲክ፣ በቆዳ ምርቶችና በሎጀስቲክስ አገልግሎት የሚሰጡ ኩባንያዎች እንደሚሳተፉ ጠቅሶ፣ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅ ለመሸጥ ብቻ ሳይሆን፣ በተለይ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በቀጥታም ሆነ በሽርክና ኢንቨስት የሚደረግባቸው ዘርፎች ስላሉ፣ ምን ዓይነት የኢንቨስትመንትና በሽርክና አብሮ የመሥራት ዕድሎች እንዳሉ ለማወቅ ጭምር መሆኑን ገልጿል፡፡  ኤግዚቢሽኑ፣ የኦማን ምርቶችን ለአፍሪካ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚ ነው ያሉት የኮሚቴው ልዑካን መሪ ዶ/ር ዋሂድ አል ካሃሩሲ፤ በኤግዚቢሽኑ የሚቀርቡ ምርቶችን የሚያመጡት በሦስተኛ ወገን በኩል በዱባይና በጅቡቲ ወደብ በኩል ነው፡፡ ወደፊት ግንኙነትና ተሳትፎአችንን በማጠንከር ሦስተኛ ወገን ሳይኖር ዕቃዎች፣ ከአንዱ አገር ወደ ሌላው በቀጥታ መግባት የሚችሉበት መንገድ መፈጠር አለበት ብለዋል፡፡ የኦፔክስ 2016 ዓላማ በኢትዮጵያና በኦማን መንግሥታት መካከል አጠቃላይ ተሳትፎን በማጐልበት በኢንዱስትሪ፣ በቴክኖሎጂና ንግድ ትብብሩ እንዲሰፋ፣ በአማንና በኢትዮጵያውያን ኩባንያዎች መካከል ትብብርና ትስስር እንዲጐለብት በማድረግ የንግድ ልውውጡ መጠን እንዲጨምር ማድረግ ነው ብለዋል፤ ዶ/ር ዋሃድ አል ካሃሩሲ፡፡ የኢትዮጵያን ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ም/ቤትን ወክለው በመግለጫው የተገኙት የንግድ ም/ቤቱ ዋና ፀሐፊ አማካሪ አቶ አዲሱ ተክሌ ም/ቤቱና መንግሥት ለኦማን የንግዱ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡", "passage_id": "2a890770362498aa322ea978f720ee5f" }, { "passage": " የህንድ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የሚያከናውኑት ኢንቨስትመንት እንዲያሳድጉ መንግስት ማንኛውንም ድጋፍ ያደርጋል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ትናንት ሲካሄድ በነበረው 9ኛው የህንድ የንግድ ፎረም ላይ ነው።ፎረሙ ከኢትዮጵያ ጋር ተሳስረን እናድጋለን በሚል መርህ የተከበረ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም የውጭ ባለሀብቶችን ለማበረታታት መንግስት ፖሊሲዎቹን በየጊዜው እያሻሻለ ነው ያሉት ከሚሻሻሉት ህጎች አንዱ የታክስ ህጉ መሆኑን በማንሳት ነው።በቅርቡ ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ በስራ ላይ እያሉ ህይዎታቸው ላለፉ 6 ህንዳውያንም ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ሀዘናቸውን ገልጸዋል።በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር ሳንጃን በበኩላቸው የህንድ ባለሀብቶች ተሳትፉ በኢትዮጵያ እያደገ መምጣቱን አንስተው በተለይ በማኒፋክቸሪንግ ዘርፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።በቅርቡ በስራ ላይ እያሉ ህይዎታቸው ያለፉ 6 ህንዳውያን ጉዳይም ረጅም ጊዜ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያና የህንድ ግንኙነት አያበላሽም ብለዋል። (ኢዜአ)", "passage_id": "ddc73d890a9721ea2644447d47ec8fca" } ]
3cf53491e3a35e8520813d27afa5091b
64b6c0f418df8a0cc1984d1c6272e712
በክልሉ በዘንድሮው መኸር ወቅት ለመሰብሰብ ከደረሰው ሰብል 94 በመቶው መሰብሰቡ ተገለጸ
ሞገስ ጸጋዬአዲስ አበባ፡- በዘንድሮው የመኸር ወቅት ከተዘሩ የተለያዩ የሰብል አይነቶች መካከል ለመሰብሰብ ከደረሰው ሰብል ውስጥ 94 በመቶ የሚሆነውን መሰብሰብ መቻሉን የኦሮሚያ ግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ጌቱ ገመቹ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የመኽር ሰብል ስብሰባን በተመለከተ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ ወደ ስራ ተገብቷል። በዚህም ወደፊት የሚደርሱ የጥራጥሬ ሰብሎች፣ እንዲሁም በአንዳንድ አከባቢዎች ዘግይተው ከሚደርሱ ሰብሎች ባለፈ፤ አሁን ለመሰብሰብ ከደረስው ሰብል መካከል 94 በመቶ የሚሆነውን መሰብሰብ ተችሏል።እንደ አቶ ጌቱ ማብራሪያ፤ አሁን ላይ የተሰበሰበው ሰብል በወቅቱ በሰብል ከተሸፈነው ከ6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር ውስጥ አምስት ሚሊዮን ሄክታር የሚሸፍን ሲሆን፤ ቀሪውን የጥራጥሬ እህልና ገና ወደ ፊት የሚደርሱ ሰብሎችን ለመሰብሰብ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።በመጀመሪያ በክልሉ ከ6 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬትን በሰብል ለመሸፈን ታቅዶ የነበረ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ጌቱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሰጡት አቅጣጫ መሰረት ጾም የሚያድር ባዶ ቦታ እንዳይኖር ታስቦ በመሰራቱ በአርሶ አደሮች፣ በኢንቨስተሮች እና መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ስር ያሉ መሬቶች እንዲታረሱ በማድረግ ወደ 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማዘጋጀት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈን መቻሉን ተናግረዋል። ከዚህም ውስጥ 191 ሚሊዮን ኩንታል እህል ለመሰብሰብ ታቅዶ አሁን ባለው የመሬት ሽፋን መሰረት ግቡን ማሳካት እንደ ተቻለ ገልጸዋል። እንደ አቶ ጌቱ ገለጻ፤ አርሶ አደሩ ልጆቹን ቤተሰቦቹን በሙሉ ይዞ እንዲሰበስብ ከክልል እስከ አርሶ አደሩ ድረስ የሚደርስ ኮሚቴ በማቋቋም አቅጣጫ ወርዶ መስራት በመቻሉ የደረሱ ሰብሎች ወቅታቸውን ጠብቀው እንዲሰበሰቡ ተደርጓል። በፍጥነትና የእህል ብክነት ሳይኖር ለመሰብሰብ ዘመናዊ ኮምባይነሮች ጥቅም ላይ ውለዋል። በተለይ የስንዴና ገብስ አምራች በሆኑ ቦታዎች በባሌ፣ በአርሲና በምዕራብ አርሲ አካባቢ በሰፊው መካናይዝድ በሆነ መንገድ እየተነሳ ነው። ይህንን ልምድ ወደ ሌላው አካባቢ በማስፋትም የደረሱ ሰብሎችን ሳይባክን ለመሰብሰብ እየሰራ ነው።ቀደም ሲል በኢንቨስተሮች እጅ የነበሩና በተያዘው አመት ብቻ ወደ ሰማኒያ የሚደርሱ ኮምባይነሮችን ለአርሶ አደሮች በማሰራጨት በጥቅሉ ከስድስት መቶ በላይ የሚሆኑ ኮምባይነሮችን ወደ ስራ በማስገባት ጥሩ ስራ ተሰርቷል። የኮምባይነሮችን ኪራይ በተመለከተም ከዚህ በፊት አንድ ኩንታል በመቶ ሃያ ብር ይሰበሰብ የነበረ ሲሆን፤ በዚህ አመት ግን በግማሽ ቀንሷል። አርሶ አደሮችም አሁን የሰብል መሰብሰብ አቅማቸው እና ዝግጁነታቸው ጥሩ እንደመሆኑ ይህን አጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል። ሰብል በሚሰበሰብበት ጊዜ በርካታ ነፍሳትና ሌሎች ፀረ ሰብል ተባዮች መኖራቸውን የሚናገሩት አቶ ጌቱ፤ አርሶ አደሩ የእህል ብክነት እንዳይኖር በጥንቃቄ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። በሐረርጌ አካባቢ ሁለተኛ ዙር የአንበጣ መንጋ ተከስቶ ከባድ ስጋትን እየፈጠረ መሆኑን በመጠቆምም፤ በባሌም እህል ገና ባልደረሰበት ሁኔታ አስፈሪ የሆነ የአንበጣ መንጋ ከሱማሌ እየገባ በመሆኑ ትልቅ ስጋት መፍጠሩን ተናግረዋል። አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37993
[ { "passage": "በአገራችን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የመኸር ምርት በ12 ዕድገት መመዝገቡን የቅድመ ምርት ግምገማ ውጤት ማሳየቱን ጠቅላይ ሚኒስትር አስታወቁ ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ዛሬ ከጋዜጠኞች ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የመኸሩ¸ምርት አሁን በደረሳቸው ቅድመ ግመገማ ግመታ መረጃ መሰረት ከ12 በመቶ በላይ ዕድገት ያሳያያል ተብሎ ይጠበቃል ፡፡ምርቱም በዋና ዋና አምራች በሚባሉ የአገራችን አከባቢዎች የሚታይ መሆኑን ጠቁመዋል ፡፡ከአጠቃላይ ግብርና ምርት የመኸሩ ብቻ 12 በመቶ ነው ያሉት አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ፤የበልግና የመስኖ ምርት በሚጨመርበት ጊዜ ከፍተኛ እንደሚሆን አመልክተዋል ፡፡ይህም አገሪቱ የግብርና ዕድገት ማሳየት ከጀመርንበት ጊዜ ጀምሮ የመጀመሪያው ትልቁ ዕድገት ተብሎ ይወሰዳል ሊሉ አስታውቀዋል ፡፡አርሶ አደሩ በአገሪቱ የነበረው የነበረው ምቹ የዝናብ ስርጭት ተጠቅሞ ያፈራውን ሰብል በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የተለያዩ ዘመናዊ የአጨዳ ማሽነሪዎችንና ከምባይነሮችን በመጠቀሙ  መሆኑን አስረድተዋል ፡፡እንደዚሁም ግብርናው ወደ መካናይዜሽን ለመለወጥ የግል ባለሃብቶች፣ መንግስት ፣የህብረት ስራ ማህበራት ማሽኖቹን ገዝተው በስፋት ያሰማሩበት ሁኔታ እንደነበረም ገልጸዋል፡፡በየገጠሩ በነበሩ አለመረጋጋቶች ምክንያት አርሶ አደሩ በምርት ተግባር ላይገባ ይችላል የሚል ግምት ነበረ ቢሆንም ፤በአብኛው ቦታ ላይ የመኸር ምርት ላይ አርሶ አደሩ በንቃት በመሳተፉ የመጣ ውጤት መሆኑን ነው ያብራሩት  ፡፡ከኢንዱስትሪ ልማት  ፍጥነት አኳያም የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ ባጠናው ጥናት መሰረት እያንዳንዱ ፋብሪካ የምርታማነት መጠን አለመቀነሱን አስታውቀዋል፡፡ እንዲያውም በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ጨምሯል ነው ያሉት ፡፡ከዛም ባለፈ 2008 ዓመተ ምህረት አዳዲስ ኢንቨስትመንት በስፋት የገቡበት ዓመት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢንዳስትሪ ፓርኮች በብዛት የገቡበተ ዓመት እንደሆነም ነው ለአብነት የጠቀሱት ፡፡በሁከቱ ሳቢያ በቃጠሎ ምክንያት ወደ ስራ ላይገቡ ይችላሉ ተብሎ የተገመቱ 26 ኢንዳስትሪዎችና የአበባ እርሻ ልማቶችም መንግስት 450 ሚሊየን ብር በመካስ በሁለት ወር ውስጥ ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረጉን አስታውቀዋል ፡፡በዚህም የተወሰነ መዛነፍ ሊኖር ይችላል ያሉት አቶ ኃይለማሪያም ፤ከአጠቃላይ የኢንዳስትሪ ሴክተር ጉዳይ ሲታይ ግን የከፋ ጉዳት ደርሷል ሊባል እንደማይችል አስረድተዋል ፡፡በአገልግሎቱ ደግሞ ገና ውጤቱ ወደፊት የሚታይ ቢሆንም በቱሪዝምና በአገልግሎት ሴክተር የተወሰነ መደናገጥ እንደነበረ ነው የገለጹት ፡፡የቱሪዝም ሴክተሩም ደረጃ በደረጃ ወደነበረበት እየተመለሰ በመሆኑ ባለፈው ሩብ በጀት ዓመት 250ሺህ ቱሪስት አገራችንን መጎብኘታቸውን ጠቅሰዋል ፡፡ይህም ዘንድሮ ከ800ሺህ እስከ 900ሺህ ቱሪስት ሊጎበኝ እንደሚችል የሚያሳይ ነው ያሉት  ፡፡ከውጭ ምንዛሬም አኳያ ኤክስፖርቱ ከዓምናው ጋር ተመሳሳይ ሆኖ እየሄደ ነው ያለው ብለዋል ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአጠቃላይ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የከፋ ጉዳት አለመድረሱን ነው ያመለከቱት ፡፡ ", "passage_id": "a608257200317542a78ee23a98ce6877" }, { "passage": "በአማራ ብሄራዊ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን በመኸር እርሻ 461 ሺ 662 ሄክታር በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ 78 ሺህ ሄክታር ማሳ በኩታገጠም ዘዴ በዘር መሸፈኑን አመልክቷል፡፡ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደሰ ግርማ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ እንደገለጹት፤ በዞኑ 461 ሺ 662 ሄክታር ማሳ በዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡ ከዚህ ውስጥ 148 ሺ ሄክታር ማሳ በዋና ዋና ሰብሎች በኩታ ገጠም ዘዴ ለመሸፈን የታቀደ ሲሆን፤ እስከ ሐምሌ 10 ድረስ በዘር ከተሸፈነው 200 ሺ ሄክታር ማሳ ውስጥ 78 ሺ ሄክታሩ በኩታ ገጠም ዘዴ በዘር ተሸፍኗል፡፡ ግቡን ለማሳካት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ሲሠሩ እንደነበር የተናገሩት አቶ ታደሰ፤ አርሶ አደሮችን በኩታ ገጠም/ክላስተር/ የማደራጀት፤ በየደረጃው ካሉ ፈጻሚ አካላት ጋር የመግባባት፤ ለአርሶ አደሮች፣ ለአመራሮችና ለባለሙያዎች ስልጠና የመስጠት ሥራ ተሠርቷል፡፡ ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ በጊዜው የማቅረብ ተግባርም ተከናውኗል፡፡ እንደ አቶ ታደሰ ማብራሪያ፤ በዞኑ በዘር ይሸፈናል ተብሎ ከታቀደው ማሳ ውስጥ 98 በመቶው አንድ ዙር ታርሷል፤ 86 በመቶ ደግሞ ሁለት ዙር ታርሷል፡፡ 58 በመቶው ደግሞ ሦስት ዙር ታርሷል፡፡ ከግብዓት አንጻር ደግሞ 344 ሺ 898 ኩንታል ሁለቱም ዩሪያና ዳፒ ማዳበሪያዎች ዞን የደረሰ ሲሆን፤ ከደሴ ወደ ሁሉም ወረዳዎች የማድረስ ሥራ እየተሠራ ነው፡፡ 332 ሺ ኩንታል ማዳበሪያ ከዞን ለህብረት ሥራ ማህበራት የደረሰ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ 300 ሺ ኩንታል ደግሞ በአርሶ አደሮች እጅ ላይ ገብቷል፡፡ 13 ሺ ኩንታል የሚሆን የስንዴ፣ የጤፍ፣ የበቆሎና የቢራ ገብስ ምርጥ ዘሮች ዞን የደረሰ መሆኑንና ከዚህ ስምንት ሺህ ኩንታል ገደማ ምርጥ ዘር በአርሶ አደሮች እጅ ላይ መግባቱን የተናገሩት አቶ ታደሰ፣ በመንግሥት የሚቀርበው ምርጥ ዘር ብቻ በቂ ባለመሆኑ 86 ሺ 98 ኩንታል የሚሆን ምርጥ ዘር አርሶ አደሩ እርስ በእርስ እንዲለዋወጥ ተደርጓል ብለዋል፡፡ በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ የ011 ቀበሌ የኩትር ጎጥ አርሶ አደር አቶ መሃመድ አበበ እንደተናገሩት፤ ካለፉት 4 ዓመታት ወዲህ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር ማሳቸውን በማቀናጀት ኩታ ገጠም እርሻ ሲተገብሩ ቆይተዋል፡፡ ይህ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ ኩታ ገጠም አስተራረስ ከመጀመራቸው በፊት ሰብሎች በጋራ ስለሚዘሩ አንዱ የሌላውን ማዕድን በመሻማት ምርታማነት እንዲቀንስ ሲያደርግ ነበር የሚሉት አቶ መሃመድ፤ ኩታ ገጠም ግን ምርታማነት እንዲጨምር ከማስቻሉም ባሻገር አንዱ ሰብል ከሌላው ጋር በመቀላቀል ይፈጠር የነበረውን ችግር ለመቅረፍ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ መሐመድ ማብራሪያ፤ አንዳንድ ሰብሎች ቀድመው ሲደርሱ ከእህል መሐል ለማውጣት አዳጋች ይሆን ነበር፡፡ ቀድሞ የደረሰውን ሰብሎ ለመሰብሰብ በሰብሎች መካከል መመላለስ የሰብል ብክነትና እንዲከሰት ሲያደርግ ነበር፡፡ ኩታ ገጠም እርሻ ከተጀመረ ወዲህ ግን የአካባቢው አርሶ አደሮች በጋራ ስለሚዘራ፣ ስለሚታረም፣ ስለሚወቃ እና ለገበያ ለማቅረብ ስለሚያስችል ተመራጭ አድርገውታል፡፡ በ2010/11 የእርሻ ዘመን ከ32 አርሶ አደሮች ጋር ማሳቸውን በማቀናጀት 32ቱ አርሶ አደሮች 32 ሄክታር ላይ ገብስ ዘርተው በሄክታር 45 ኩንታል ገብስ ማምረትም ችለዋል፡፡ ከ32 አርሶ አደሮች ጋር በክላስተር በመደራጀት ዘንድሮም በ32 ሄክታር ማሳ ላይ ሙሉ ፓኬጅ በመጠቀም በክላስተር ሰንዴ ዘርተዋል፡፡ ሌላኛው የለጋምቦ ወረዳ የ011 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ካሳ መኮንን እንደሚሉት ከ15 አርሶ አደሮች ጋር ማሳቸውን በማቀናጀት ባለፈው ዓመት ስንዴ በዘሩበት ማሳ ላይ ዘንድሮም በኩታ ገጠም ገብስ ዘርተዋል፡፡ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ አራት ጊዜ በማረስ ማሳቸውን ሲያዘጋጁ በነበረው አንድ ሄክታር ማሳ ላይ 1 ኩንታል ዩሪያና ዳፕ ተጠቅመው በመስመር ዘርተዋል፡፡ በሄክታር እስከ 35 ኩንታል ምርት ለማግኘት እቅድ እንዳላቸው የተናገሩት አቶ ካሳ፤ እቅዳቸውን ለማሳካት ከባለሙያዎች የተሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦችን በሙሉ ተግባራዊ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል፡፡ በዞኑ በ2010/2011 የምርት ዘመን 10 ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ምርት የተሰበሰበ ሲሆን በ2011/12 የምርት ዘመን የምርት መጠኑን በ23 በመቶ በማሳደግ 12 ነጥብ ሁለት ሚሊየን ኩንታል ለማምረት መታቀዱን ከዞኑ የግብርና መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡አዲስ ዘመን ሐምሌ 12/2011መላኩ ኤሮሴ", "passage_id": "7bd43b6f97a9b4f84609a3320bc30235" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥር 3 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ ባለፈው መኸር በ13 ነጥብ 4 ሚሊየን ሄክታር መሬት ከለማው ሠብል በዘጠኝ ሚሊየን ሄክታር ላይ የነበረው መሰብሰቡን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።", "passage_id": "0f68c34f6bcea7758bf0436ba6103af7" }, { "passage": "-ግብርናው አደጋ ላይ መውደቁ ተገልጿልበአዳማ ከተማ ለሁለት ቀናት እየተካሄደ በሚገኘው የግብርና ዘርፍ የከፍተኛና የታችኛው እርከን አመራር አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ፣ በመጪው ዓመት ከዋና ዋና ሰብሎችና ከአገዳ እህሎችና ከሌሌችም የግብርና ውጤቶች 406 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ኡመር ሑሴን እንደገለጹት፣ በዚህ ዓመት 306 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኝቷል። የታቀደው ከ370 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚገኝ ነበር። ይህም ሆኖ በ2012 ዓ.ም. ከ400 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መመረት እንዳለበት ገልጸዋል።በኢትዮጵያ ግብርና መስክ ትኩረት ይሰጣቸዋል ከተባሉ መካከል ስንዴና በቆሎ ምርት ላይ ሞዴል አርሶ አደሮች በሔክታር የሚያመርቱትን መጠን በአገር ደረጃ ለማምረት ጥረት ይደረጋል ብለዋል።በሌላ በኩል በየጊዜው እያሽቆለቆለ የመጣው የግብርና ዘርፍ ዕድገት፣ በአሁኑ ወቅት የ5.7 በመቶ ዕድገት ማሳየቱ በአምስቱ ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ ከተቀመጠው የስምንት በመቶ ዝቅተኛው ዓመታዊ የዕድገት ርከን ያነሰ መሆኑ አሳሳቢ ነው ብለዋል። ይህ የዕድገት ምጣኔ ግን እየተካሄደ በሚገኘው የቅድመ ምርት ዘመን ግመታ ወደ 2.8 በመቶ ዝቅ ሊል እንደሚችል አመላካች ሥጋቶች በመኖራቸው፣ \"የአደጋ ጊዜ ጥሪ\" ማስተጋባት የሚያስፈልግበት ወቅት ነው ብለዋል። በተለይም በጥራጥሬ ሰብሎች ምርት ላይ የ5.2 በመቶ፣ በቅባት እህሎች መስክም የ10 በመቶ የምርት ዕድገት ቅናሽ እንደሚኖር በግብርናው ላይ የተደረጉ ጥናቶች ማመላከታቸው ተጠቅሷል።ግብርናው ባልተለመዱ አዲስ የሰብልና የእንስሳት በሽታዎች እየተጠቃ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ የአፈር ለምነትም በሥጋት ቀለበት እንደገባ ጠቅሰዋል። ዝናብ በሚኖርበት ወቅት ጨዋማነት፣ እርጥበት በማይኖርበት ወቅትም አሲዳማነት ከ17 ሚሊዮን በላይ አነስተኛ አርሶ አደሮችን ህልውናና ምርታማነት የሚፈትኑ ሆነዋል።እንዲህ ያሉ ችግሮችን ቢያስተናግድም፣ በአነስተኛ ገበሬው ዘንድ በሔክታር እስከ 40 ኩንታል፣ ሞዴል በሚባሉት ገበሬዎች ዘንድ እስከ 100 ኩንታል በሔክታር እየተመረተ የሚገኘውን ስንዴ አማካዩን ምርት በአገር ደረጃ ማምረት ከተቻለ ስንዴ ከውጭ ማስመጣት እንደሚቀር ሚኒስትር ኡመር ገልጸዋል።እንዲህ ያሉ የግብርናውን ስንክሳሮች የሚመክረው የመሪዎች ስብሰባ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ሥር በተዋቀረ ግብረ ኃይል የሚመራ እንደሆነ ሲገለጽ፣ ከወረዳና ቀበሌ ጀምሮ እስከ ምክትል ጠቅላይ ሚስትር ደመቀ መኮንን ያሉ አመራሮች ለግብርናው ዘርፍ አጣዳፊና ዘላቄ መፍትሔ በማበጀት በተለይ በክረምቱ የመኸር ወቅት ከፍተኛ ምርት እንዲገኝ የሚሠሩ ሥራዎች ዘመቻ ይካሄዳል ተብሏል።", "passage_id": "71088482b3e16f7e1b1793439833e2fc" }, { "passage": "በዘንድሮው የመኸር ወቅት 19 ሚሊየን ኩንታል የሰብል ምርት እንደሚጠበቅ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኢዶሳ ጊቢሳ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት ከምርት ስብሰባ በፊት በተሰሩት ግምገማዎች መሰረት ከማሽላ፣ ባቄላና ሰሊጥ ሰብሎች ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ27 በመቶ ብልጫ ያለው ምርት ይጠበቃል፡፡እንደ አቶ ኢዶሳ ገለፃ ክልሉ ከ790,000 ሄክታር በሚሆን መሬት 20 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡የግብርና ቢሮው የክልሉን ምርታማነት ለማሳደግ ለአምራቾች ሥልጠናዎችን ጨምሮ ከፍተኛ እገዛ ሲያደርግ  እንደነበርና ይህም ውጤታማ እንዳደረገው ታውቋል፡፡ባለፈው ዓመት በድርቅ ተጎድቶ የነበረውን የእርሻ ቦታ አስፈላጊውን የግብርና ግብዓት በማሟላት በዚህ የመኸር ወቅት ከባለፈው ዓመት በ4.5 በመቶ የበለጠ የእርሻ መሬት በሰብል ምርት  የተሸፈነ መሆኑ ተገልጿል፡፡ባለፈው ዓመት በተከሰተው ድርቅ በአጠቃላይ 10.2 ሚሊየን የሚሆን ህዝብ ለድርቅ ተጋላጭ እንደነበረ አቶ ኢዶሳ አስታውሰው፣ በክልሉ ደግሞ 11 ወረዳዎች የድርቁ ተጋላጭ እንደነበሩም ጠቁመዋል፡፡በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘንድሮ ከሚጠበቀው ምርት የ13 ሚሊየን ኩንታል ምርት ከፍጆታ አልፎ ለገበያ ይቀርባል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ከምግብ አቀነባባሪ ፋብሪካዎች ጋር የገበያ ትስስር ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል፡፡ትርጉም -ሰለሞን ተስፋዬ ", "passage_id": "8a08203e8ae99605e4f07586c972b92b" } ]
9a8833fe90311d45b9ce27747a854085
d4438579e7dfea0f49a6653558b63f31
አትክልት ተራው ወደ ኃይሌ ጋርመንት መዛወሩ ለግብይትም ሆነ ለሕግ ማስከበር ስራ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ ተገለጸ
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡-መንግስት ማግኘት የሚገባውን ገቢ ለማግኘት፣ የግብይት ሁኔታ ምቹ ለማድረግ እንዲሁም ውጤታማ የገቢ ሕግ የማስከበር ሥራ ለማከናወን የአትክልት ተራው ወደ ኃይሌ ጋርመንት መዛወር ጠቃሚ እንደሆነ የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ቢሮ የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ ኮማንደር አህመድ መሃመድ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት በከተማ አስተዳደሩ ጥላ ሥር የከተማዋ፣ የክልልና የፌደራል ነጋዴዎች ተሰባጥረው የሚሰሩ በመሆኑ በሕገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ የሚደረገውን ቁጥጥር አዳጋች አድርጎታል።እንደ ኮማንደር አህመድ ገለጻ፤ አንድ የአዲስ አበባ ገቢዎች የሕግ አስከባሪ አካል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ነጋዴ ነው ብሎ ሕግ ሲያስከበር ከጎኑ ያለው ነጋዴ በፌደራል ሥር ከሆነ በዝምታ የሚያልፍበት ሁኔታ ይታያል። በተመሳሳይም የፌደራል ነጋዴውም ሕገ ወጥ ስራ እየሰራ አንተ የአዲስ አበባ ነህ፣ አንተ የኦሮሚያ ነህ አይመለከትህም የሚል አስተሳሰብ ስለነበረ ችግሩ ውስብስብ ነው ያሉት ኮማንደር አህመድ፤ ሕግ የማስከበር ተግባር በአንድ ቢሮ ብቻ የሚፈታ ስላልሆነ የበርካታ አካላትን ተሳትፎና ቅንጅት የሚጠይቅ ነው ብለዋል።ኮማንደር አህመድ እንደገለጹት የሁሉም የሕግ አስከባሪ ስራ አላማ ሕገ ወጥ ንግድን መግታት ቢሆንም በጋራና በመናበብ የመስራት ልምድ ባለመዳበሩ ክፍተቶች ይታያሉ። ክፍተቶቹ የተፈጠሩት ከክፋት ሳይሆን ከአሰራር ክፍተት ነው። ለምሳሌ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ተግባሩ ተፅፎ ሲሰጠው “እነዚህን ጉዳዮች ትሰራለህ፣ ሕግ ታስከብራለህ፣ ገቢ ትሰበስባለህ” ተብሎ ስለሆ ከተሰጠው ሕግ የማስከበር ስራ ውጪ ሌሎች ነጋዴዎችን የሚከታተልበት አግባብ አይኖርም። ስለዚህ ሁሉም የራሱን ግብር ከፋዮች እየለየ ይሰራል። ይህ ሁኔታ ለሕግ ማስከበሩ ፈታኝ በመሆኑ የጋራ ህብረት ፈጥሮ በትብብር መስራት ይገባል።እንደ ኮማንደሩ ገለጻ በከተማ አስተዳደሩ በነበረው የአትክልት መሸጫ ቦታ ሕጋዊ ሆኖ የመሸጥ ሁኔታው ብዙም አልነበረም። በዚህ ሁኔታ ደግሞ ከገቢ አንፃር ሲታይ ነጋዴው ሲሸጥ ደረሰኝ እየቆረጠ መንግስት ማግኘት የሚገባውን ገቢ እያስገኘ ነበር ማለት ያስቸግራል። ምክንያቱም ቦታው አንዱ ሸጦ የሚሄድበት፣ ሌላው ተቀምጦ የሚሸጥበት፣ ከፊሉ ደግሞ ቆሞ የሚስተናገድበት የተዘበራረቀ ሁኔታ በመኖሩ ለመቆጣጠር አመቺ አልነበረም። በዚህ ሁናቴ የሕግ አካላት ንግድ ፈቃድ ያለውና የሌለውን ለመለየት የሚቸገሩበት ሁኔታ በመኖሩ አሰራሩን ዘመናዊ ማድረግ የግድ እንደሆነ ኮማንደር አህመድ ተናግረዋል።ይህንን ታሳቢ በማድረግም የአትክልት ተራው ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ በዘመናዊ መንገድ ወደ ተደራጀው ቦታ በመዛወሩ ለቁጥጥርና ለክትትል አመቺ ሁኔታ መፈጠሩንና እያንዳንዱ ነጋዴም ቁጥር ተሰጥቶት የንግድ ፈቃዱን ማሳየት በሚችልበት አግባብ ተደራጅቶ እንቅስቃሴውን መለየት በሚያስችል መንገድ መሰራቱን ኮማንደሩ ገልፀዋል።በመጨረሻም የንግዱ ማህበረሰብ የትም ሆኖ ይሰራ የትም ንግድ ፈቃድ ኖሮት ሕጋዊ ሆኖ እንዲሰራ ማድረግ የገቢዎች ህግ የማስከበር ተግባር ነው የሚሉት ኮማንደር አህመድ፤ ማንኛውም ነጋዴ ህጋዊ ሆኖ ለሚሸጠው ነገር ደረሰኝ እየቆረጠ የሚጠበቅበትን ግዴታ መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38005
[ { "passage": "አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 19 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የገበያ ቁጥጥርን በማጠናከር እና የግብይት ሰንሰለቱን ስርዓት በማስተካከል ከአምራች ወደ ሸማች በቀጥታ በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ እንደሚገባ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገለጹ።ምክትል ከንቲባዋ በጦር ኃይሎች አካባቢ አዲስ የተገነባውን አሙዲ ፕላዛ ኩዊንስ ሱፐር ማርኬት ጎብኝተዋል።በጉብኝቱም ላይ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት÷ የነዋሪውን የገበያ ፍላጎት ለሟሟላት የምርት አቅርቦት መጨመርና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረቡ በከተማዋ የሚታየውን ለኑሮ ውድነት ለመቀነስ ያግዛል ብለዋል።በሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች የግብይት ሰንሰለቱን በማሣጠር ከአምራች ወደ ሸማች በቀጥታ ለማቅረብ የሚተጉ ድርጅቶችን የሚያደርጉትን ጥረት የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንም ገልፀዋል።አሙዲ ፕላዛ ኩዊንስ ሱፐር ማርኬትን ጨምሮ ሌሎች መሰል ሱፐር ማርኬቶች ለነዋሪው የዕለት ተዕለት ህይወት አስፈላጊ የሆኑ ምርቶችን በማምረት በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ እንዲያቀርቡ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አክለው ተናግረዋል።በጉብኝቱ ላይም ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው እስከ ከፍተኛ ገቢ ያላቸው ነዋሪዎች ሲገበያዩ መመልከታቸውም ተገልጿል።ሸማቾቹም የሱፐር ማርኬቱ በአካባቢያቸው መከፈት የተለያዩ ምርቶችን በፈለጉበት ሠዓት በአንድ ቦታና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ እንደረዳቸው መግለጻቸውን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕሬስ ሴክሬተሪያት ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።\nየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "af1d19c37a2dab6a2b07ccfb2a4f0deb" }, { "passage": "በድሬዳዋ የአትክልት ውጤቶችና የጫት ግብይትና ኣጠቃቀም የኮሮና ቫይረስ ከመከሰቱ በፊት ከነበረው እምብዛም ለውጥ ያልታየበት ነው ተብሏል።ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ኅብረተሰቡ የአትክልት ውጤቶችን በጥንቃቄ እንዲጠቀም፣ ጫትንም ቢቻል እንዲተው ካልሆነ ግን እያጠበ እንዲጠቀም መክሯል። አስተዳደሩ የግብይት ሥርዓቱ ይሻሻላል ብሏል።\n", "passage_id": "ec7ccce676e257365fc8b71204ac4300" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ህዳር 30፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከጽዳት ባለሙያዎችና ከጃንሜዳ አካባቢ ማህበረሰብ ጋር በመሆን አካባቢውን የማፅዳት ስራ አከናውነዋል።በጃንሜዳ ውስጥ ያሉ አትክልት ነጋዴዎች ከጥቂት ቀናት በኋላ ወደ ተዘጋጀላቸው የአትክልት መሸጫ ስፍራዎች እንደሚዘዋወሩ ወ/ሮ አዳነች ተናግረዋል ።ጃንሜዳን ለጥምቀት በዓል ዝግጁ ለማድረግ እና ወደ ቀድሞ አገልግሎቱ ለመመለስ በተከታታይ የማጽዳት ስራ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ምክትል ከንቲባዋ ገልጸዋል ።ሸማቹን እና አምራቹን አንድ ላይ ማገናኘት የሚያስችሉ የአትክልት እና መሰል መገበያያ ስፍራዎች በየክፍለ ከተማው ተደራሽ የማድረግ ስራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ወ/ሮ አዳነች ጠቁመዋል፡፡ነጋዴውም ሆነ ነዋሪው ህብረተሰብ ጃንሜዳን ወደ ቀድሞው አገልግሎቱ ለመመለስ በሚደረገው ጥረት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ምክትል ከንቲባዋ ጥሪ ማቅረባቸውን ከከተማው ፕሬስ ሰክሬታሪያት ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!", "passage_id": "7a03828fae2cdbeb4b9a535294aee987" }, { "passage": "አዲስ አበባ:- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአራዳ ክፍለ-ከተማ ባቋቋመው ግብረ ኃይል “ህገ- ወጥ” ያላቸውን የንግድ እንቅስቃሴዎች በመቆጣጠርና የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ ህገ-ወጥ የንግድ አሰራርንና ደላላ መር የንግድ እንቅስቃሴን ሥርዓት ለማስያዝ ታስቦ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ። ሰሞኑን በአዲስ አበባ በተለያዩ መውጫና መግቢያ በሮችና አትክልት ተራ ላይ በሌሊት በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ፣ ቁጥጥርና ክትትል በህገ ወጥ መንገድ የንግድ ተግባራትን ሲያከናውኑ የተገኙት ነጋዴዎች ለተፈጠረው ከነፃ ገበያ ስርአት ተፃራሪ የሆነና ደላላ መር የዋጋ ንረት አስተዋፅኦ ሲያደርጉ የነበሩ መሆናቸውን ከክፍለ-ከተማው የሥራ ኃላፊዎች የተገኘው መረጃ አመላክቷል። የአራዳ ክፍለ ከተማ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደሳለኝ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፣ የተያዙት ምንም አይነት ፍቃድ ሳይኖራቸው ወደ አዲስ አበባ ለመግባት የሞከሩና በየመንገዱ ሲሸጡ የተገኙ ህገ-ወጥ ነጋዴዎች ናቸው። “እነዚህ ሰዎች በዋናነት አራት ዋና ዋና ጥፋቶችን ፈፅመዋል” የሚሉት አቶ ሀብታሙ ጥፋቶቹም ግብይት በደረሰኝ መሆን ሲገባው ይህን አለማድረግ በዚህም መሰረት ከግብር ስወራ ጋር የተያያዘ ወንጀል መፈጸም፣ያለ ንግድ ፍቃድ መነገድ፣ የንግድ አድራሻ አለመኖርና ከአድራሻ ውጪ መነገድ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌለው የዋጋ ጭማሪ ማድረግ ናቸው። እንደ አቶ ሀብታሙ ገለጻ እርምጃው በጥናት ላይ የተመሰረተና ከሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶችና   ተቋማት ከተውጣጡ ሰዎች በተቋቋመ ግብረ ሀይል አማካኝነት ተጠንቶ የተወሰደ ነው። እርምጃውን ተከትሎ ያለውን ሂደት አስመልክቶ እንደተናገሩትም “የተያዙት ንብረቶች ይወረሱና ይተመናሉ፣ በተተመነው መሰረትም በሸማቾች አማካኝነት ለህብረተሰቡ ይሸጣሉ። በሽያጭ የተገኘው ገንዘብም በመንግሥት አደራ የሂሳብ መዝገብ ውስጥ ይቀመጣል” ብለዋል። “ከተወሰደብን በኋላ\nመልሰን እንድንገዛ እድል\nሊሰጠን አልቻለም፣ የተያዘው\nንብረትም ለህብረተሰቡ ይሸጣል\nተብሎ በእጅ አዙር\nለሌሎች ነጋዴዎች እየተሸጠ\nነው።” በሚል ለአዲስ\nዘመን የቀረቡ አቤቱታዎችን\nበተመለከተም አቤቱታው ስህተት\nመሆኑን የሚገልፁት ኃላፊው\n“ለነጋዴ አልተሸጠም በሸማቾች\nስር የተቋቋሙ ዩኒየኖች\nስላሉ ለእነሱ ነው\nየሚሸጠው። የመንግሥት የልማት\nድርጅት የሆነው ኢትፍሩትም\nአንዱ ገዥ ነው።\nእነዚህም በተመጣጠነ ዋጋ ለህብረተሰቡ የሚያቀርቡ መሆናቸው ስለተረጋገጠ ነው እንዲገዙና እንዲሸጡ የተደረገው” ብለዋል። እነዚህ ህገ-ወጥ ነጋዴዎች ህብረተሰቡን ከመጉዳታቸው ጎን ለጎን ህጋዊውን ነጋዴም እየጎዱትና የነፃ ገበያ ሥርዓቱንም እያበላሹት ነው የሚገኘው በመሆኑም ይህ እርምጃ እነዚህ ወገኖች ወደ ውድድር እንዲገቡ፣ ሁሉም ሰው ንግድ ፍቃድ አውጥቶ እንዲሰራ፣ ግብር ስወራ እንዲቆም፣ ነጋዴዎች አድራሻ ኖሯቸው እንዲሰሩና በገበያ ህግ እንዲመሩ የሚያደርግ ነው የሚሉት አቶ ሀብታሙ፤ ህብረተሰቡም የደረሰኝ ግብይትን ተግባራዊ እንዲያደርግና ህገ ወጥ ነጋዴዎችን በማጋለጥ ከመንግሥት ጎን እንዲቆም ጥሪ አስተላልፈዋል። በአሁኑ ወቅት ምንም አይነት ኢኮኖሚያዊ ምክንያት በሌለው የዋጋ ንረትና እሱን ተከትሎ የተፈጠረው የኑሮ ውድነት በህዝብ ዘንድ በከፍተኛ ደረጃ የመወያያ ርዕሰ ጉዳይ ከመሆን ባለፈ ምሬት እየፈጠረ እንደሆነ ይታወቃል።አዲስ ዘመን መስከረም 12/2012ግርማ መንግሥቴ ", "passage_id": "20833bc28915837cb8753766296e5035" }, { "passage": " የአትክልት ተራ ገበያ ማዕከል ነጋዴዎች በማዕከሉ ከፍተኛ የሆነ ሕገወጥ ንግድ መንሰራፋቱን፣ በገበያ ማዕከሉ ያለውን ችግር ለመቅረፍ የተቋቋመው ግብረ ኃይል ችግሩን ከመቅረፍ ይልቅ የችግሩ መንስዔ እየሆነ ነው ሲሉ ወቀሱ፡፡በማዕከሉ የንግድ ማከናወኛ ቦታ ይዘውና ንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱ ነጋዴዎች ቁጥር ከሦስት መቶ በላይ ቢሆንም፣ በየቀኑ አንድ ሺሕ የሚሆኑ ሕገወጥ ነጋዴዎች በገበያ ማዕከሉ መሀል መንገድ ላይ ያለ ደረሰኝና ሥርዓት በጎደለው መንገድ ንግድ ሲያከናውኑ፣ የተቋቋመው ግብረ ኃይል ከማስቆም ይልቅ ከለላ እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡የገበያ ማዕከሉ ነጋዴዎች አቤቱታ ለማቅረብ ተፈራርመው ለሚመለከታቸው የአራዳ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች ቢያስገቡም ምላሽ አለማግኘታቸውን ይገልጻሉ፡፡ቅሬታቸውን ለሪፖርተር ያቀረቡት ነጋዴዎቹ፣ ‹‹ግብረ ኃይሉ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ በአትክልት ተራ የገበያ ማዕከል በከፍተኛ ሁኔታ ሕገወጥ ነጋዴ እንዲበራከት አድርገዋል፡፡ ለሕገወጥ ነጋዴ በተደራጀ መንገድ ሽፋን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ በዚህ የተነሳም ችግር ውስጥ ወድቀናል፤›› ብለዋል፡፡የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በዚሁ የገበያ ማዕከል ደረሰኝ የሚቆረጥበት ሕጋዊ ንግድ እንዲኖር ማድረጉ ተገቢ መሆኑን በበጎነት የጠቀሱት ነጋዴዎቹ፣ አትክልትና ፍራፍሬ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሥርዓት ውስጥ እንዲገባ መደረጉ ግን አግባብ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡አግባብ ያልሆነ የታክስ ዓይነት ተጥሎባቸውም ቢሆን ያለ ደረሰኝ ሕገወጥ ንግድ እያንቀሳቀሱ የሚገኙ ከአንድ ሺሕ በላይ ነጋዴዎችን ግብረ ኃይሉ ቸል ማለቱ የሕጋዊ ነጋዴዎችን ህልውና እየተፈታተነው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የመብትና የሕግ ጥያቄ የሚያነሱ ነጋዴዎችም በግብረ ኃይሉ በኩል ምላሽ ማግኘት ሲገባቸው እየታሠሩ ነው ብለዋል፡፡በአራዳ ክፍለ ከተማ የንግድ መምርያ ኃላፊ አቶ በፈቃዱ ሰለሞን ጉዳዩን በተመለከተ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ የአትክልት ተራ የንግድ እንቅስቃሴ በሕግ እንዲመራ ለማድረግ ሥራዎች መጀመራቸውን፣ ከእነዚህም መካከል አንዱ የደረሰኝ ግብይት መሆኑን ጠቅሰው ይህ ተግባራዊ በሚሆንበት ጊዜ የተለያዩ ችግሮች ጎን ለጎን መከሰት መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡በዋናነት የንግድ ማዕከሉ በደረሰኝ እንዲሠራ የተፈለገበት ምክንያት አዲስ አበባ የምታገኘውን አትክልትና ፍራፍሬ ከ75 በመቶ በላይ የሚያቀርበው ይህ ማዕከል በመሆኑ ነው ብለው፣ ይህ ማዕከል ያለ ደረሰኝ መሥራቱ በአጠቃላይ የሆቴልና የሬስቶራንት ንግድ የታክስ ሥርዓት ላይ ችግር መፍጠሩን ጠቁመዋል፡፡በአጠቃላይ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ አራት አጀንዳዎች መለየታቸውን፣ ከፌዴራል ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንና ከንግድ ሚኒስቴር ጋር በመሆን በቅርቡ ነጋዴዎችን ያሳተፈ ውይይት እንደሚካሄድ ጠቁመዋል፡፡   ", "passage_id": "ccac354db2bf693944f5c89cc7ba8129" } ]
fe96355341fe431ee2b886cb6e3cd1c2
8ddfe9980f30d234c091be647f4edd58
የጋዜጠኛ እና አርቲስት ኢብራሂም ሀጂ አሊ ስርአተ ቀብር ተፈጸመ
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ስር የሚታተመው በሪሳ ጋዜጣ በ1968 ዓ.ም ስራ ሲጀምር ከነበሩት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የነበሩት ጋዜጠኛ፣ አርቲስት እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ዕድገት ውስጥ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተው ኢብራሂም ሀጂ አሊ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ።ኢብራሂም ሀጂ አሊ ካለፈው ክረምት ጀምሮ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ የህክምና ክትትል ሲደረግለት ቆይቶ ትናንት ሌሊት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ይታወሳል። የቀብር ስነስርዓቱም ትናንት 9፡00 ሰዓት ላይ ቤተሰቦቹ፣ የስራ ባልደረቦቹ የሙያ አጋሮቹ እንዲሁም አድናቂዎቹ በተገኙበት በኮልፌ የሙስሊም መቃብር ተፈጽሟል።በ1968 ዓ.ም በሪሳ ጋዜጣ ስራ ሲጀምሩ ኢብራሂም ሀጂ አሊ አንደኛው ጋዜጠኛ ነበረው ጋዜጠኛ፣ አርቲስት እና የቋንቋ ተመራማሪው በሙዚቃ ህይወቱ በርካታ ነጠላ ዜማዎችን ያበረከተ ሲሆን፣ አራት ዓይነት የሙዚቃ መሳሪያዎችን መጫወት ይችል ነበር። ኢብራሂም ሀጂ አሊ ሙዚቃን የጀመረው ተወልዶ ባደገበት በድሬዳዋ ሲሆን በ1967/68 የአርፈን ቀሎ ባንድ 2ኛ ትውልድ በመባል በሚጠራው ከአዱ ቢራ ባንድ መስራቾች ከሚባሉት የክብር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ፣ ሂሜ የሱፍ፣ አብዱ ሸኩር፣ መሀመድ ጠዊል ጋር በመሆን አንደኛው መስራች ነበረ።ከዚያን ጊዜ በኋላ የጋዜጠኝነት ህይወትን እስከሚቀላቀል የአፋን ኦሮሞ ሙዚቃን በኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢዎች ለማስተዋወቅ እድል አግኝቶ ተጠቅሞበታል። ኢብራሂም የግጥም እና ዜማ ደራሲ እንደነበረም በቅርብ የሚያውቁት እና የእርሱን ስራዎች የተጫወቱ ይመሰክሩለታል።በ1987 ዓ.ም ሬዲዮ ፋና ሲመሰረት ፋናን ከተቀላቀሉ አንጋፋ ጋዜጠኞች መካከልም አንደኛው ሲሆን፤ ተወዳጅ የሆነውን ፋና አፋን ኦሮሞ ፕሮግራምን አዘጋጅቶ በማቅረብም ይታወቃል። ኢብራሂም በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እስከ ኤዲተርነት ያገለገለ ሲሆን ህይወቱ እስከሚያልፍ ድረስም የስፖርት ጋዜጠኛ ነበር። አፋን ኦሮሞ በጥናት ላይ ተመስርቶ እንዲያድግም ጥረት ካደረጉ ታላላቅ ሰዎች መካከል አንደኛው እንደሆነ የዘገበው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38008
[ { "passage": "በአሶሳ ስታዲየም ለሰዓታት በህዝቡ ስንብት ከተደረገለት በኋላ በከተማዋ በሚገኝ የሙስሊም መካነ መቃብር ቀብራቸው ተፈፅሟል።በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ ቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድራን እና የከተማው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።የአቶ አህመድ አስከሬን ከህንድ ትናንት ማለዳ ላይ ነበር አዲስ አበባ የገባው።ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አቀባበል አድርገዋል።ለ8 አመታት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልን በርዕሰ መስተዳድርነት የመሩት አቶ አህመድ ናስር ባጋጠማቸው የኩላሊት ህመም ሳቢያ በህንድ ሃገር በህክምና ሲረዱ ቆይተዋል።ከትናንት በስቲያ ሌሊትም በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።በርዕሰ መስተዳድርነት ዘመናቸው የክልሉን ሰላም ከማረጋገጥና ልማት ከማምጣት አንጻር ከፍተኛ ስራን ማከናወናቸው ነው የተነገረው።አቶ አህመድ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባትም ነበሩ።በርዕሰ መስተዳድሩ ሞት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እና ብሔራዊ ክልሎች ሃዘናቸውን በመግለፅ ለቤተሰብ እና ለክልሉ ህዝብ መፅናናትን ተመኝተዋል።(ኤፍ ቢ ሲ) ", "passage_id": "e051a73502eab4617086caeb7208aa4f" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2006/ዋኢማ/ የፀረ- ድህነት ትግሉና ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱ ትክክለኛ አቅጣጫ እንዲመራ የፀና አቋም በመያዝ ሲታገሉ የነበሩት ታጋይ አለማየሁ አቶምሳ የቀብር ስነ ስርዓት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ተፈፀመ።በስርዓተ ቀብሩ ስነ-ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት፣ ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።የታጋይ አለማየሁ አስከሬን የፖሊስ የማርሽ ባንድ ታጅቦ ወደ ቅድስት ካቴድራል ቤተክርስቲያን ከሄደ በኋላ የፀሎት ስነ-ስርዓት ተደርጎለታል።የአራት ልጆች አባት የሆኑት አቶ አለማየሁ አቶምሳ በ1961 ዓ.ም ከአባታቸው ከአቶ አቶምሳ ሚጃና እና ከእናታቸው ከወይዘሮ አየለች ብሩ በምስራቅ ወለጋ ዞን ቢሎ ቦሼ ወረዳ የተወለዱ ሲሆን፤ በተወለዱ በ45 ዓመታቸው የካቲት 29 ቀን 2006 ዓ.ም በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ስርዓተ ቀብራቸው ተፈፅሟል።ጣጫ እንዲመራ የፀና አቋም በመያዝ ሲታገሉ የነበሩት ታጋይ አለማየሁ አቶምሳ የቀብር ስነ ስርዓት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ተፈፀመ።በስርዓተ ቀብሩ ስነ-ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት፣ ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።የታጋይ አለማየሁ አስከሬን የፖሊስ የማርሽ ባንድ ታጅቦ ወደ ቅድስት ካቴድራል ቤተክርስቲያን ከሄደ በኋላ የፀሎት ስነ-ስርዓት ተደርጎለታል።የአራት ልጆች አባት የሆኑት አቶ አለማየሁ አቶምሳ በ1961 ዓ.ም ከአባታቸው ከአቶ አቶምሳ ሚጃና እና ከእናታቸው ከወይዘሮ አየለች ብሩ በምስራቅ ወለጋ ዞን ቢሎ ቦሼ ወረዳ የተወለዱ ሲሆን፤ በተወለዱ በ45 ዓመታቸው የካቲት 29 ቀን 2006 ዓ.ም በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ስርዓተ ቀብራቸው ተፈፅሟል።", "passage_id": "fe3045663876cfe7461aa1135534a74a" }, { "passage": "የ1440ኛው የዒድ አልአድሀ (አረፋ) በዓል በመላ አገሪቱ  በደማቅ ስነ ስርዓት ተከበረ፡፡የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተወካይ ሼህ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በበዓሉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ለአገራችን አንድነትና ለሰላም፣ ለአብሮነት በጉልበታችን፣ በእውቀታችንና በገንዘባችን የሚፈለግብንን ሁሉ ማበርከት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡በበዓሉ ላይ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ በበኩላቸው፣ የአረፋ በዓል ለመላው የሙስሊም ማህበረሰብ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሳብ እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አስተዳደር የሙስሊሙን ጥያቄ ለመመለስ የሚያደርገው ጥረት የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በዘላቂነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ተወካይ አቶ ዮሃንስ ምትኩ በዓሉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የዘንድሮን የዒድ አልአድሀ በዓል ልዩ የሚያደርገው የሙስሊሙ አንድነት ከወትሮው በተለየ መልኩ የተጠናከረበት፣ በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድና በሃይማኖት አባቶች ያጋራ ጥረት በሰላማዊ መንገድ ልዩነቶች የጠበቡበትና መቻቻል በታየበት ወቅት በድምቀት መከበሩ ነው ብለዋል፡፡(ኢቢሲ) ", "passage_id": "3bc9ae773b775ca0df8d5e347aad23fd" }, { "passage": "ለበርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ ዳኝነት ታሪክ ውስጥ ጨዋታ ከመምራት አንስቶ የጨዋታ ታዛቢ በመሆን እና በርካታ ዳኞችን አስተምሮ በማብቃት የሚታወቁት ብርቱዉ ሰው ዓለም ንፀብህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።በኢንተርናሽናል ዳኝነት ዘመናቸው በተለያዩ ከፍተኛ ውድድሮች ላይ በብቃት ያዳኙት ጋሽ ዓለም ንፀብህ ያለፉትን ዓመታት ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት በአልጋ ላይ በመሆን ህክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ዛሬ ንጋት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።የእኝህ ታላቅ ዳኛ የቀብር ሥነ ስራዐት ዛሬ ታህሳስ 26 ቀን በ09:00 በቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት የሚፈፀም ይሆናል።ሶከር ኢትዮጵያ በቀድሞ አንጋፋ ዳኛ ህልፈት የተሰማትን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀች ለቤተሰቦቻቸው፣ ለባልደረቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናትን ትመኛለች።", "passage_id": "80fef6f7594230e04cddb245be331be3" }, { "passage": "ልኡልና አልጋወራሽ መሐመድ ቢን ሳልማን\n\nዶ/ር ሰአድ አልጃብሪ ለደኅንነታቸው በመስጋት ካናዳ የተጠለሉ ሰው ናቸው። ዶ/ር ሰአድ አልጀብሪ በተለይ ከእንግሊዙ የስለላ መዋቅር ኤም16 ጋር በመተባበር የሽብር ጥቃቶችን በማክሸፍ ስራቸው ይታወቃሉ። ወደ ካናዳ የሸሹት የዛሬ 3 ዓመት ሲሆን አልጋ ወራሹ ቢን ሳልማን ግን እርሳቸውን ወደ አገር ቤት ለማምጣት ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም ተብሏል።\n\nአሁን ደግሞ በርሳቸው ላይ ከፍተኛ ጫና ለመፍጠር ሳኡዲ የሚገኙ ልጆቻቸው በአገሪቱ የጸጥታ ኃይል እንዳሳገቱባቸው ቤተሰባቸው ይፋ አድርጓል። የበኩር ልጃቸው ካሊድ አልጃብሪ ለቢቢሲ እንደተናገረው ኦማርና ሳራ የሚባሉትን ወንድምና እህቱን በቁጥጥር ሥር ለማዋል 50 የሳኡዲ የጸጥታው መስሪያ ቤት ባልደቦች በ20 መኪናዎች ተጭነው ወደ ቤታቸው መጥተዋል።\n\nካሊድ አልጃብሪ (ግራ) ታናሽ ወንድሙ ኦማር (ቀኝ) በአገሪቱ መንግሥት ታፍኖ ይገኛል ይላል።\n\nሪያድ የሚገኘው የቤተሰቡ መኖርያ የደኅንነት ካሜራዎችን ምስል የያዙ የምስል ቅጂ ቋቶች ተነቃቅለው መወሰዳቸውን፣ ከፍተኛ ብርበራ መካሄዱን፣ የ20 እና የ21 ዓመት እድሜ ያላቸው ወንድም እህቱም ወዳልታወቀ ስፍራ እንደተወሰዱ አብራርቷል።\n\nየዶ/ር ሰአድ አልጃብሪ የበኩር ልጅ ካሊድ ከአባቱ ጋር ጥገኝነት ከጠየቀበት ካናዳ በመሆን ለቢቢሲ እንደተናገረው ይህ ሁሉ እየተደረገ ያለው አባቱ ላይ ጫና በመፍጠር ወደ አገር ቤት ለማስመለስ ነው። ካሊድ ጨምሮ እንደገለጸው ወንድምና እህቱ አሁን በሕይወት ስለመኖርቸው እንኳ እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይችልም።\n\nሳራ አልጃብሪም በመንግሥት ተይዛለች ተብሎ ይታመናል\n\nቢቢሲ ስለ ጉዳዩ የሳኡዲ መንግሥትን ምላሽ ለማካተት ያላሰለሰ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካለተም። \n\nዶ/ር አልጃብሪ በሳኡዲ የደኅንነት መዋቅር ውስጥ ባገለገለበት ዘመን አል-ቃኢዳን ለማንበርከክ ሁነኛ ሚና የነበረው ሰው እንደሆነ ይነገራል። በተለይም ከአሜሪካ፣ ካናዳ፣ እንግሊዝ፣ አውስትራሊያና ኒዊዚላንድ የደኅንነት መሥሪያ ቤቶች ጋር እጅና ጓንት በመሆን በርካታ ውጤት ያስመዘገበ ሰው ነበር። በፈረንጆች በ2010 እርሱ የደረሰበት መረጃ አል-ቃኢዳ በአውሮፓ ከባድ የሽብር ጥቃት ከማድረሱ በፊት እንዲከሽፍ ምክንያት ስለመሆኑም ይመሰከርለታል።\n\nዶ/ር ሰአድ አልጃብሪ (ፊታቸው የተከበበው) እአአ 2015 ላይ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ባቀኑበት ወቅት በወቅቱ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስትሯ ቴሬሳ ሜይ አቀባበል ተደርጎላቸው ነበር\n\nበየመን ይገኝ የነበረው አል-ቃኢዳ መጠኑ ከፍ ያለ ቦምብ በእቃ መጫኛ አውሮፕላን አስርጎ ማስገባቱን፣ አውሮፕላኑም ወደ ቺካጎ እንደሚበርና ቦምቡ የሚገኘው በማተሚያ ማሽን ውስጥ እንደሆነ የተብራራ መረጃን ለእንግሊዙ የኤም 16 ያቀበለውም ዶ/ር ሰአድ አልጃብሪ እንደሆነ አንድ የዩናይትድ ኪንግደም የደህንት ባለሞያ መስክረዋል።\n\nበማተሚያ ማሽን ተጭኖ የነበረው ቦምብ ቺካጎ ደርሶ ቢሆን ኖሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ አሜሪካዊያንን ሕይወት ይቀጥፍ ነበር ብለዋል እኚህ የደህንነት ሰው። አልጃብሪ ዝምተኛና የተረጋጋ ሰው ሲሆን በአርተፊሻል ኢንተሌጀንሲ የዶክትሬት ዲግሪውን ከኤደንበርግ ዩኒቨርስቲ አጊንቷል።\n\nከዚያ በኋላ ወደ ሳኡዲ በመመለስ የደኅንነት መስሪያ ቤቱን ማዘመን ችሏል። \"ሳኡዲዎች ከርሱ በፊት የደህንነት ስራ ይሰሩ የነበረው ኋላ ቀር በሆነ መንገድ ሰዎችን አሰቃይቶ እንዲናዘዙ በማድረግ ነበር። እርሱ ይህን ሁኔታ ለውጦታል፤ መረጃን በኮምፒውተር በመጥለፍ ዘመናዊ ስለላን ለሳኡዲ ያስተዋወቀ ሁነኛ ሰው ነበር\" ይላሉ ስማቸው ያልተገለጸ የምዕራቡ አገር የደኅንነት ሰው።\n\nበ2015 ንጉሥ አብደላ መሞታቸውን ተከትሎ ግማሽ ወንድማቸው ሣልማን ቢን አብዱልአዚዝ ንግሥናውን ሲቆጣጠሩ... ", "passage_id": "f0033321b15e98349564a0665d2197d0" } ]
55fb472f719fe88719e18a7586d5a9fa
1f2eae0dd35e237436a3e0f8fd100620
በቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናት ላይ የተሰጠው ውሳኔ የሕግ ጥሰት እንደሌለበት ተገለጸ
አዲሱ ገረመው አዲስ አበባ፡- ከፍተኛው ፍርድ ቤት በትላንትናው ዕለት በቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናትን በአመክሮ እንዲለቀቁ ያሳለፈው ውሳኔ የትኛውንም ወገን እንደማይጎዳና የህግ ጥሰት እንደሌለበት ተገለጸ። የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኮሎኔል ብርሃኑ ባዬ እና ኤታማዦር ሹም የነበሩት ሌፍተናንት ጄኔራል አዲስ ተድላ ላይ የተሰጠው ውሳኔ ለኢትዮጵያ ቀጣይ ጉዞ የሚኖራቸው አንድምታ ከፍተኛ መሆኑም ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በሰብዓዊ መብት መርኅ አስተሳሰብ የሞት ቅጣት በጣም ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ስለሚያስከትል ወደ እድሜ ልክ እሥራት መቀየሩ ተገቢና ፍትሐዊ እርምጃ ነው። በቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናት ላይ የተወሰነው ፍርድም ሕጉን ተከትሎ የተፈጸመ ሂደት ነው። እድሜ ልክ ቅጣት የሚፈረድበት ሰው 20 ዓመታት ከታሰረ በኋላ በአመክሮ ሊለቀቅ እንደሚችል የሚደነግግ ሥርዓት በመኖሩ ውሳኔው ማንንም የማይጎዳና የሕግ ጥሰትም የሌለበት ነው።እንደ ዶክተር ዳንኤል ገለጻ፤ የቀድሞ መንግስት ባለ ሥልጣናት የነበሩ ሰዎች በፍርድ ቤት ጥፋተኛነትና የቅጣት ውሳኔ ከተወሰነባቸው በኋላ የሞት ቅጣት ወደ እድሜ ልክ እስራት ሲቀየር የመጀመሪያው አይደለም። ከዚህ በፊትም የእስር ዘመናቸውን ጨርሰው የተለቀቁ ብዙ ታሳሪዎች የሞት ቅጣቱ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተቀይሮላቸው ነው የእስር ዘመናቸውን ያጠናቀቁትና ከእስር የወጡት።በሰብዓዊ መብት መርኅ ደግሞ የሞት ቅጣት ወደ እድሜ ልክ እሥራት መቀየሩ ተገቢ እርምጃ እንደሆነ ይታመናል። ምክንያቱም የሞት ቅጣት በጣም ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ስለሚያስከትል በተለይ ረጅም ጊዜ ለታሰሩ ሰዎች ወደ እስር መቀየሩ ተገቢና ፍትሐዊ እርምጃ ነው። ስለዚህ እርምጃው ሕጉን ተከትሎ የተፈጸመ ሂደት ነው።ዶክተር ዳንኤል እንደሚሉት፤ በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ የሀሳብ ልዩነት ቢኖር አያስገርምም። ምክንያቱም ሁልጊዜም ቢሆን በዳኝነት ላይ ሦስት ዳኞች ሲሰየሙ ዳኞች የተለያየ አተረጓጎም ሊኖራቸው ስለሚችል ካልተስማሙ በአብላጫ ድምጽ ይወሰናል። እናም የአብላጫ ድምጽ ውሳኔው የሞት ቅጣቱ ወደ እድሜ ልክ እስራት እንዲቀየር መደረጉ፤ እድሜ ልክ ቅጣት የሚፈረድበት ሰው 20 ዓመት ከታሰረ በኋላ በአመክሮ ሊለቀቅ እንደሚችል የሚደነግግ ሥርዓት አለ። ከዚህ በፊት የተለቀቁት ብዙ የደርግ ባለሥልጣኖችም በዚሁ አይነት ሁኔታ ነው የተለቀቁት። ስለዚህ ይሄም ብዙ የተለየ አይሆንም።ምናልባት ይሄን ከዚህ በፊት ከነበሩት ለየት የሚያደርገው አሁን ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሰዎች መንግስት እስር ቤት ውስጥ ሳይሆን ይሄንን 20 ዓመት ያሳለፉት ኤምባሲ ቅጥር ጊቢ ውስጥ መሆኑ ነው። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ የነበሩበት ሁኔታ ከእስር ጋር የሚመሳሰል መሆኑን መሠረት አድርጎ ነው ውሳኔውን ያሳለፈው።ይሁን እንጂ ከዚህ በፊት እንደተለቀቁት የደርግ ባለስልጣናት በተለቀቁበት ወቅት ጥያቄ አስነስቶ ነበር። ከተጎጂ ቤተሰቦች አንጻር የዚህ አይነት ጥያቄ በተወሰነ መጠን ሊነሳ እንደሚችል ይገመታል። ነገር ግን ሁሉም የተጎጂ ቤተሰቦች አንድ ዓይነት ስሜትና አስተያየት አላቸው ማለት አይደለም። አንዳንድ የተጎጂ ቤተሰቦች ይሄን ያህል እስር ከተፈጸመ በቂና ተመጣጣኝ ቅጣት ነው፤ ከዚህ የበለጠ እስር ቤት መታሰር የለበትም የሚል አስተያየት ያላቸው ሰዎች ይኖራሉ። አንዳንድ የተለያየ አስተያየት ያላቸው ሰዎች ደግሞ ሊኖሩ ይችላል። ሁሉንም ሰው በእኩል ደረጃ ያስደስታል ተብሎ ባይታሰብም፤ በአብዛኛው አስተሳሰብ አንድ ሰው በጥፋቱ 20 ዓመት ያህል ከታሰረ ለጥፋቱ ተመጣጣኝ የሆነ ቅጣት አግኝቷል፣ ታርሟል፣ ተስተካክሏል ተብሎ ይገመታል።በመሆኑም በተመሳሳይ ሁኔታ ከ20 ዓመት በላይ ታስሮ ምህረት ሳያገኝ በእስር ላይ የሚገኝ ሰው ካለ ተፈጻሚ መሆን ይኖርበታል። ነገር ግን የፍርድ ምርመራቸውን ያልጨረሱ ሰዎች ይኖራሉ። ምክንያቱም አንዳንዶቹ መጀመሪያ የታሰሩ ሰዎች ሁሉ ሲታሰሩ አንድ ላይ የታሰሩ ሳይሆን በኋላ እየዘገዩ የታሰሩ ሰዎች አሉ። ከውጭ ሀገርም ታስረው የመጡ ሰዎች አሉ። ስለዚህ  እነሱ ቅርብ ጊዜ ስለነበረ የታሰሩት፤ ይሄ 20 ዓመት የሚለው ጊዜ ወይም የተፈረደባቸው የእስር ዘመን ገና አልሞላ ይሆናል። ስለዚህ ያ አንድ ሰው የተፈረደበትን የእስር ዘመን መጠበቁ የግድ ይላል።እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ዶክተር ጥበበ የማነብርሀን የኢትዮጵያ እርቀ ሠላም ኮሚሽን አባል ኮሚሽነር በበኩላቸው እንደሚሉት፤ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት የነበሩት ኮሎኔል ብርሃኑ ባዬ (በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩ) እና ሌፍተናንተ ጄኔራል አዲስ ተድላ (በወቅቱ ኤታማዦር ሹም የነበሩ) በጣሊያን ኤምባሲ የነበራቸው ከ29 ዓመታት በላይ ቆይታ በእስር ቤት ካለው ሁኔታ የማይተናነስ በመሆኑና መብታቸው ተገድቦ በመቆየቱ በአሁኑ ጊዜ ያለው የጤንነታቸው ሁኔታ እንዲሁም የዕድሜያቸው መግፋት ካሳለፉት የማህበረሰብ የመገለል ጊዜ አንፃር ጋር ተዳምሮ ከፍተኛ የሆነ የአካልና የስነ ልቦና ጫና አሳድሮባቸው ነበር።ስለሆነም ከሰብዓዊ ርህራሔ መብት አንፃር እና ያሉበትን ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት በአመክሮ ምህረት ተደርጎላቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲገናኙ መንግስትን እንድንጠይቅላቸው በተደጋጋሚ በቤተሰቦቻቸው በኩል ጥያቄ ቀርቦ ነበር። መንግስትም ጉዳዩን በሕግ አግባብ ለመፍታት የቀረበውን ጥያቄ ለማስተናገድ የሔደበትን ርቀት የሚደነቅ ነው። በተለይም ለክብርት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለፍትህ አካሉና ለጠቅላይ አቃቢ ሕግ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል።መሰል ተግባራት ለሀገራችን ቀጣይ ጉዞ የሚኖራቸው አንድምታ ከፍተኛ እንደሚሆን በማመን፤ ለዚህ ሂደት መሳካት በተለየ አግባብ ለኮሚሽናችን ድጋፍ ላደረጉ አካላት ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን ያሉት የዓለም ሎሬት ዶክተር ጥበበ፤ በሀገራችን ኢትዮጵያ እርቀ ሰላም ለማስፈን ለምናደርገው ጉዞ አንድ እርምጃ ከፋች እንደሚሆን እናምናለን ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38059
[ { "passage": "በሶማሌ ክልል የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ሰብሳቢ የክልሉ ፕሬዚዳንት ነበሩየፌዴራልም ሆኑ የክልል ዳኞች የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በሕገ መንግሥቱ ከፍተኛ ኃላፊነት የተጣለባቸው ቢሆንም፣ የዳኝነት ነፃነታቸው በአስፈጻሚውና በሌሎች አካላት ጣልቃ ገብነት ምክንያት በመገደቡ ገለልተኛ እንዳልነበሩ፣ ዜጎችም በዳኝነት አካሉ ላይ አመኔታ እንዳይኖራቸው ማድረጉን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተናገሩ፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳኝነት ሥራ አስተዳደር የሚያጋጥሙ ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮችን እየፈተሸ መፍትሔ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ ጉባዔ በአዋጅ ቁጥር 25/88 ከአንቀጽ 31 እስከ 34 ድንጋጌ መሠረት ያቋቋመና በዓመት አንድ ጊዜ ጉባዔ ማድረግ እንዳለበት የተደነገገ ቢሆንም፣ በ25 ዓመታት ውስጥ ሦስተኛውን ጉባዔ እሑድ ታኅሳስ 21 ቀን 2011 ዓ.ም. አድርጓል፡፡ ፕሬዚዳንቷ ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የጉባዔው ሦስተኛ ዓመታዊ ስብሰባ ሲካሄድ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፣ ጉባዔው ዕቅድ አዘጋጅቶና የሚመራበትን ደንብ አውጥቶ ወደ ሥራ በመግባት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት አሠራርን ለማሻሻል የሚረዱ አቅጣጫዎችን የማመላከት፣ የዳኝነት ሥርዓቱን ነፃ፣ ግልጽና የተቀላጠፈ ለማድረግ የሚያግዙ ተግባራትን የማከናወን ኃላፊነት ተሰጥቶት እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ጉባዔው በ27 ዓመታት ውስጥ ሁለት ጊዜ ብቻ መሰብሰቡንና ላለፉት 25 ዓመታት ሳይሰበሰብ መቅረቱን ጠቁመው፣ ይኼም የዳኝነት ነፃነት የሚጋፋ አሠራር እንዲበራከትና ዜጎችም በዳኝነት አካሉ ላይ አመኔታ እንዳይኖራቸው ማድረጉን አስረድተዋል፡፡ የፍርድ ቤቶች ታሪክ እንደሚያስረዳው የዳኝነት አገልግሎቱ ፍትሕ ተደራሽ እንዲሆን ሲሠራ የነበረ ተቋም ቢሆንም፣ ባለፉት ዓመታት የዳኝነት አካሉ ነፃነትና ገለልተኛነቱ በመጣሱ፣ ፍርድ ቤቶች ከመዳከማቸውም በላይ ኅብረተሰቡ በፍርድ ቤቶች ላይ ያለው እምነት እንዲሸረሸር ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ የመንግሥት ኃላፊዎች ስለዳኝነትና ገለልተኛነት ግንዛቤ አለመኖር፣ በዳኞች ምልመላና ሹመት ላይ ክፍተት መኖሩ፣ ዳኞች የሚጠየቁበት ግልጽ መመዘኛ አለመኖር፣ የሥነ ምግባር ችግርና የተጠናከረ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ሥራ አለመሠራቱ ችግሩ ተባብሶ እንዲቀጥል ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡ ፕሬዚዳንቷ ጉባዔውን ከከፈቱ በኋላ የጉባዔው አባላት የሆኑት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የበላይ አመራሮች፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና ሁሉም የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ፕሬዚዳንቶች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡የዳኝነት ችግር ሥር የሰደደ መሆኑን የገለጹት የጉባዔው ተሳታፊዎች፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች የሚጋጥሟቸው ችግሮችን ገልጸዋል፡፡ ከችግሮቹ መካከል ጭብጥ የመለየት ችግር፣ አቤቱታውን ተቀብለው ረዥም ጊዜ ካቆዩ በኋላ አያስቀርብም ብሎ መዝጋት፣ በማይነበብ ጽሑፍ ውሳኔ መጻፍ፣ የሥራ ቋንቋቸው አማርኛ ያልሆኑ ክልሎች የሚሰጡትን የፍርድ ቤት ውሳኔ በባለሙያ ባለመተርጎማቸው የትርጉም መጣረስና ሌሎች በርካታ ችግሮች እንደሚገጥማቸው አስረድተዋል፡፡ ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሚደርሱ አቤቱታዎች በአብዛኛው ከመሬት ባለቤትነት ጋር የተገናኙና በአርሶ አደሮች የሚቀርቡ በመሆናቸው፣ ክልሎች የሚሰጡትን ፍርድ ለማስተርጎም በገጽ 50 ብር እየከፈሉ ማስተርጎም ስለማይችሉ ይኼም አንዱ ችግር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ የመጨረሻና ውሳኔውም እንደ ሕግ የሚቆጠር ቢሆንም፣ ክልሎች በተለይ የኦሮሚያ ፍርድ ቤቶች ውሳኔውን ባለመቀበልና የውሳኔ መዝገቡን ባለመጥቀሳቸው አቤቱታዎች በብዛት ወደ ሰበር ችሎት እየመጡ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ተመሳሳይ ክሶችን ባጭሩ ምላሽ ለመስጠት ትርጉም የተሰጠባቸውን የሰበር መዝገቦች በመጥቀስ ችግሩን ማቃለል ሲቻል፣ ‹‹አልታዘዝም›› ባይነት በመብዛቱ ችግሩን እያባባሰው መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ በመሆኑም የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች ግንኙነትና አሠራር ሊፈተሽ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ የዳኝነት ሥርዓቱን ሊመራ የሚችል ተቋም አስፈላጊ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የክልልም ሆነ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችና ዳኞች ወጥ አሠራር እንዲኖራቸው፣ ተቋማዊ የአቅም ግንባታና የጋራ ሥልጠና አስፈላጊ መሆኑንም አባላቱ ተናግረዋል፡፡ የክልል ፍርድ ቤቶች፣ በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤትን የሚታይን ክስ፣ የክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤቶችና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትን ክስ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች በውክልና እንደሚያዩና ጉዳዮቹም የብሔር ግጭት፣ የታክስና ሌሎች  መሆናቸውን አስታውሰው፣ በዚህ አሠራር ዙሪያም ችግሮች ስላሉ ሊፈተሽ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡ ተዘዋዋሪ ችሎት ከፌዴራል ወደ ክልል የሚሄደው በየሦስት ወራት በመሆኑ ዜጎች የተፋጠነ፣ ነፃና ቀልጣፋ ፍትሕ የማግኘት ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው እየተጨፈለቀ መሆኑን፣ በተለይ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ፕሬዚዳንቶች ተናግረዋል፡፡ በክልል የሚገኙ አብዛኞቹ ዳኞች የተማሩት መንግሥት በሚያውቃቸውና ዕውቅና ባላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ሳይሆን፣ በግልና ብዙም ዕውቅና በሌላቸው  ዩኒቨርሲቲዎች በመሆኑ፣ የአጻጻፍና የተለያዩ ሕግ ነክ ጉዳዮች ላይ የሚሰጡ ውሳኔዎችና ትዕዛዞች ላይ ችግር እንደሚከሰትም ጠቁመዋል፡፡ በጀትን በሚመለከት የፌዴራልም ሆነ የክልል ፍርድ ቤቶች ችግር እንዳለባቸው ጠቁመው፣ በክልል ምክር ቤቶችና በፓርላማ የሚፀድቅላቸው በጀት በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ቢሆንም፣ የሚሰጣቸው ግን 300,000 ብር ብቻ መሆኑን ገልጸው፣ በቂ እንዳልሆነና ቀሪውን ማን እንደሚወስደው ግራ እንደገባቸው ተናግረው እንዲታሰብበት አሳስበዋል፡፡ ጣልቃ ገብነትን በሚመለከት የጋምቤላ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት፣ ከመዝገብ ጋር በተገናኘ በቀጥታ ጣልቃ ገብነት ነበር ብለዋል፡፡ የክልሉ ፕሬዚዳንት፣ ‹‹እኔ ያሰርኩትን ለምን ትፈታለህ? ማን ሥልጣን ሰጠህ?›› የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው እንደነበርም ገልጸዋል፡፡ አሁን ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ቀድሞ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ስለነበሩ፣ በሕግ ጉዳይ ላይ ጣልቃ እንደማይገቡ እምነታቸው መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ሁሉም ክልሎች በተለይ ከ2010 ዓ.ም. እስከ 2011 ዓ.ም. አራተኛ ወር ድረስ ያከናወኗቸውን ሥራዎች ገልጸዋል፡፡ የሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ለየት ያለና ሁሉንም ያስገረመ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ የክልሉ ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ሰብሳቢ ፕሬዚዳንቱ አቶ አብዲ መሐመድ (አብዲ ኢሌ) እንደነበሩ ገልጸው፣ ምን ያህል ጣልቃ ገብነት እንደነበር አሳይተዋል፡፡ በሰርተፍኬት ደረጃ የሚሠሩ ዳኞች በክልሉ እንደነበሩና አሁን በሪፎርሙ እያስተካከሉ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከሁሉም ክልሎች የተሻለና ለፌዴራል ፍርድ ቤቶችም ጭምር ተምሳሌት መሆን አለበት የተባለ አደረጃጀትና አጠቃላይ አሠራር መዘርጋቱን ያስታወቀው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በፕሬዚዳንቱ የቀረበው ሪፖርት ሁሉንም ያስደመመና በፕሬዚዳንቷ ጭምር ምሥጋና የተቸረው ነበር፡፡ አስተያየት የሰጡ አንዳንድ የጉባዔው ተሳታፊዎች ያነሱት ጥያቄ በሁሉም የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቶች ላይ ጣልቃ መገባት እንደሌለበት አስረግጠው ሲናገሩ፣ የዳኝነት ነፃነት መከበር እንዳለበትና እስከ መጨረሻው ይኼ ቁርጠኝነት መቀጠል ስለመቻሉ ነበር፡፡ በአጠቃላይ ጉባዔው ሙሉ ቀን ውይይት ካደረገ በኋላ ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል፡፡ ዳኞች ነፃነታቸውን ማስጠበቅ እንዳለባቸው፣ ጉባዔው መደበኛ ሆኖ በየዓመቱ መካሄድ እንዳለበት፣ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች በክልሎች መተግበር እንዳለባቸው የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ፕሬዚዳንቶች ኃላፊነት መውሰዳቸውን፣ የክልል ፍርድ ቤቶች የፌዴራል ጉዳዮችን በውክልና ስለሚያዩ የበጀት ድጋፍ እንዲደረግላቸውና በሌሎችም አቋሞች ላይ በመስማማት አጠናቀዋል፡፡", "passage_id": "181b75f36899b56150b444809c1715f0" }, { "passage": "እሑድ መጋቢት 18 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰማያዊ ፓርቲ የሥነ ሥርዓት ኮሚቴ የተላለፈውን አምስት የፓርቲውን አባላት የማሰናበትና የማገድ ውሳኔ፣ ረቡዕ መጋቢት 21 ቀን 2008 ዓ.ም. ስብሰባ ያካሄደውና ውሳኔውን የመረመረው የፓርቲው ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን በሥነ ምግባር ኮሚቴው የተላለፈውን ውሳኔ አገደ፡፡ የኮሚሽኑ ሰብሳቢ አቶ አበራ ገብሩ ለሪፖርተር ዕገዳውን አረጋግጠዋል፡፡‹‹በዚህ ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ከሚመለከተው አካል ከመገለጹ በፊት ውሳኔው በተለያየ መንገድ በመሰማቱ፣ በውሳኔ አሰጣጡ ሒደት ላይ አንዳንድ ችግሮች በመኖራቸው፣ እንዲሁም ከታገዱት አባላት መካከል ይግባኝ ያስገባ በመኖሩ ምክንያት ውሳኔው ተግባራዊ እንዳይሆን አግደነዋል፤›› ሲሉ አቶ አበበ የዕግዱን ምክንያት ገልጸዋል፡፡የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ከቻለባቸው ምክንያቶች በዋነኛነት ውሳኔው ከፓርቲው ሕገ ደንብ ጋር የሚጣረስ በመሆኑ፣ ግልጽ ያልሆነ ነገር በማካተቱና አስፈላጊውን የሥነ ሥርዓት ሒደት ስላልተከተለ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡በዚህም መሠረት ግልጽ ያልሆነ ነገር አለው የሚለውን በተመለከተ፣ ‹‹ተባረዋል የተባሉት አባላት ገንዘብ አጥፍተዋል ከሚል ክስ በስተቀር ተከሳሾቹ በስንት ብር ተጠያቂ እንደሆኑ በግልጽ የሚገልጽ ነገር የለም፡፡ በፓርቲው ደንብ መሠረት የፓርቲውን ሊቀመንበር በተመለከተ የመጨረሻውን ውሳኔ የሚሰጠው አካል ጠቅላላ ጉባዔው በመሆኑ ውሳኔው የመተዳደሪያ ደንቡን ጥሷል፡፡ እንዲሁም የውሳኔው ሒደት የሥነ ሥርዓት ጉድለት አለው ሲባል ደግሞ ተከሳሾች በሌሉበት ምስክሮች መሰማታቸው አግባብ ስለሌለው ነው፤›› በማለት አቶ አበራ አብራርተዋል፡፡ከላይ በተገለጹት ምክንያቶች ኮሚሽኑ በአመራሮቹ ላይ የተወሰደውን ዕርምጃ ማገዱን ገልጸዋል፡፡ ‹‹ጉዳዩን እየመረመርን ስለሆነ በራሳችን የማጣራት ሒደት ጉዳዩን አጣርተን የራሳችንን ውሳኔ በ15 ቀናት ውስጥ የምንሰጥ ሲሆን፣ እኛ የምንሰጠው ውሳኔም የመጨረሻው ይሆናል፤›› በማለት አክለዋል፡፡ኮሚሽኑ በተላለፈው ውሳኔ ላይ ጣልቃ የመግባት ሥልጣን አለው ወይ የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ሰብሳቢው፣ ‹‹የሥነ ሥርዓት ኮሚቴው ውሳኔ የመጨረሻ ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን ሰዎች ይግባኝ ሲሉና ምናልባት መስመሩን የለቀቀና ሥነ ሥርዓት ያልተከተለ ነገር አለ ተብሎ ሲገመት፣ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ጉዳዩን የማየት ሥልጣን ይኖረዋል፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ በአንቀጽ 11 ንዑስ አንቀጽ 8 ላይ ለኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን የተሰጠውን ሥልጣንና ኃላፊነት ይገልጻል፡፡ በዚህም መሠረት፣ ‹‹የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን በሥነ ሥርዓት ኮሚቴ የተሰጡ ውሳኔዎችን ይግባኝ ይመረምራል፡፡ የመጨረሻ ውሳኔም ይሰጣል፤›› በማለት አስቀምጧል፡፡ይህ ሥልጣን በፓርቲው ደንብ መሠረት እንደተሰጣቸው የሚገልጹት ሰብሳቢው፣ ‹‹የእኛ ውሳኔ የሥነ ምግባር ኮሚቴውን አቅም አልባ እንዳደረገው የሚገለጹት ነገሮች መሠረተ ቢስ ናቸው፤›› በማለት ተቃውሞአቸውን አሰምተዋል፡፡‹‹ለሥነ ሥርዓት ኮሚቴው ክብር አለን፡፡ አባላቱ ሥራቸውን በአግባቡ እንደሠሩም እናምናለን፡፡ ሥራቸውን በሚሠሩበት ወቅት ግን የተወሰኑ ችግሮች ነበሩ፡፡ እነዚያ ችግሮች ደግሞ በውሳኔው ላይ ተፅዕኖ ይፈጥራሉ ብለን በማመናችን እንደገና ጉዳዩን ለማየት አግደነዋል እንጂ፣ እነርሱ ሥራቸውን በሚገባ ለመሥራት ጥረት አድርገዋል፤›› በማለት አስተያየታቸውን ቋጭተዋል፡፡አምስት አባላት ያሉት የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን በጠቅላላ ጉባዔው ይቋቋማል፡፡ ተጠሪነቱም ለጠቅላላ ጉባዔው ሲሆን የሚከተሉት ሥልጣንና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፡፡ የፓርቲው ገንዘብና ንብረት በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን መከታተልና መቆጣጠር፣ በፓርቲ ውስጥ የሚከሰቱ የአባላትም ሆነ የአመራር አካላት የሥነ ሥርዓት ጉዳዮችን የሚያይ የሥነ ሥርዓት ኮሚቴ ማቋቋም፣ እንዲሁም ከአባላት የሚቀርቡ ቅሬታዎችንና ጥቆማዎችን መሠረት በማድረግ የአሠራር ጉድለቶች በወቅቱ እንዲታረሙና ችግሮቹም እንዲፈቱ ጥረት ማድረግ የሚሉ፣ ወዘተ ናቸው፡፡ ", "passage_id": "170a4397becac988f84a2f73a993754e" }, { "passage": "የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ክልል መንግሥት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳያደርግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ አሳለፈ፡፡ምክር ቤቱ ውሳኔውን ያሳለፈው ነሐሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. አድርጎት በነበረው አስቸኳይ ጉባዔ፣ በትግራይ ክልል የሚካሄደው ምርጫ እንዳልተደረገና እንደማይፀና ያስተላለፈው ውሳኔ ተጥሶ በማግኘቱ መሆኑን ትናንት ማምሻውን በመንግሥት መገናኛ ብዙኃን አሳውቋል፡፡ምክር ቤቱ ያስተላለፈውን ውሳኔ ሲከታተል የነበረው የሕገ መንግሥት ጉዳዮችና የማንነት ጉዳዮች አጣሪ ኮሚቴ፣ ክልሉ የፌዴሬሽኑን ውሳኔ ባለማክበሩና ባለመፈጸሙ፣ ትናንት መስከረም 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ባደረገው መደበኛ ስብሰባው፣ የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ክልል መንግሥት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳያደርግ ውሳኔ ማሳለፉን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ምክር ቤቱ በትግራይ ክልል መንግሥት ላይ ሦስት ውሳኔዎችን ማሳለፉን የገለጸ ሲሆን፣ የመጀመርያው ክልሉ ያካሄደውን ኢሕገ መንግሥታዊ ምርጫን ተከትሎ ከተመሠረቱ፣ የትግራይ ክልል ምክር ቤትና ከፍተኛ የሕግ አስፈጻሚ አካላት ጋር፣ የፌዴራል መንግሥት ምንም ዓይነት ግንኙነት አያደርግም፡፡ ሁለተኛው ውሳኔ ደግሞ የፌዴራል መንግሥት የትግራይ ሕዝብን የልማትና መሠረታዊ አገልግሎቶች ፍላጎትን ማዕከል በማድረግ፣ የከተማና የቀበሌ አስተዳደርን ጨምሮ፣ በክልሉ ከሚገኙ ሕጋዊ ተቋማት ጋር ብቻ የሥራ ግንኙነት እንደሚያደርግ ወስኗል፡፡ በመጨረሻም የውሳኔውን አፈጻጸም በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔና ጉዳዩ በሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴ ክትትል መደረግ እንዳለበትም ምክር ቤቱ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ትናንት መስከረም 26 ቀን 2013 ዓ.ም.፣ የ2013 ዓ.ም. መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሂድ፣ ሪፖተር ጋዜጣን ጨምሮ የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን የተገኙ ቢሆንም፣ ስብሰባው በዝግ እንደሚካሄድ ተነግሮ እንዳይገቡ ተከልክለዋል፡፡ ሆኖም ግን በዕለቱ አመሻሹ ላይ ምክር ቤቱ ከላይ የተገለጹትን ውሳኔዎች ማሳለፉን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል፡፡  ", "passage_id": "cf5ed046324f164767b0a1bff5d42eff" }, { "passage": "ክራውን ሆቴልና ሲክስ ኮንቲኔንትስ ሆቴልስ ኢንክ ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ጽሕፈት ቤት እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስ ክርክር ባደረጉት “CROWN HOTEL” እና “CROWN PLAZA” የንግድ ምልክት ጉዳይ፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል ተባለ፡፡ሰበር ሰሚ ችሎቱ የመጨረሻውን ውሳኔ የሰጠው ከሐምሌ ወር 1987 ዓ.ም. ጀምሮ “CROWN HOTEL” የሚለውን የንግድ ስያሜ፣ በኢትዮጵያዊ አዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ጽሕፈት ቤት አስመዝግበው እያሳደሱ ሲጠቀሙበት የቆዩትና እየተጠቀሙበት ያሉት የሆቴሉ ባለቤት ወይዘሮ ዘውዲቱ መስፍን መሆናቸውን ነበር፡፡በሰበር የመጨረሻ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ለሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ያመለከተው ሲክስ ኮንቲኔንትስ ሆቴል ኢንክ (Six Continents Hotels Inc.) ነው፡፡ ጸሜክስ ግሎባል ኢንተርፕራይዝ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ልደታ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ባለ ሰፊ ቦታ ላይ እየገነባው ለሚገኘው ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል “CROWN PLAZA” የሚለውን የንግድ ስያሜ ለመጠቀም ከአገሪቱ ኢንቨስትመንት ጋር በቀጥታ የተገናኘ ቢሆንም፣ ሰበር ችሎቱ ግን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 80(3ሀ) ላይ የተሰጠውን ሥልጣን ተላልፎ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠቱ ተገቢ እንዳልሆነ ሲክስ ኮንቲኔንትስ ሆቴልስ ኢንክ በማመልከቻው ገልጿል፡፡ሲክስ ኮንትኔንትስ በጸሜክስ ግሎባል በኩል እንዲሰጠው በተደጋጋሚ ያመለከተው “CROWN PLAZA” የንግድ ስያሜ “CROWN HOTEL” በሚል ስያሜ ቀድሞ መመዝገቡንና ተመሳሳይ በመሆኑ እንደማይፈቀድለት በየደረጃው ሲወሰንበት የመጣ ቢሆንም፣ የመጨረሻና የማያዳግም ዕልባት ለማግኘት ወደ ሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ አመልክቷል፡፡አጣሪ ጉባዔው የቀረበለትን የማመልከቻ ሰነድ ተመልክቶ በሰጠው አስተያየት እንደገለጸው፣ የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የሰላም የዴሞክራሲ የኢኮኖሚ፣ ፖለቲካና ማኅበራዊ ዕድገትን በማሳካት፣ አንድ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ የመገንባት ዓላማዎችና እምነቶች መያዙን በግልጽ አስፍሯል፡፡ ይህ ዕውን የሚሆነው ከማንም በላይ ሥር ሰዶ ያለውን ድህነት በመዋጋትና በመቅረፍ ነው፡፡ ከዚህ ጎል ለጎን ደግሞ ተጨማሪ ሥራዎችን መሥራት ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች ውስጥ የባለሀብቱ አቅምና ብዛት አነስተኛ በሆነበት ሁኔታ ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንት ዋናው መሆኑን አብራርቷል፡፡በሕገ መንግሥት አንቀጽ 41(1-7) 43(1) ላይ እንደተደነገገው፣ የአገሪቱ ሕዝቦች የማያቋርጥ ዕድገት የማግኘት መብታቸውን መንግሥት ማረጋገጥ የሚችለው አዳዲስ ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንት በማስፋፋት፣ ዓመታዊ ግብር በመሰብሰብና ተጨማሪ የሥራ መስኮች እንዲፈጠሩ በማድረግ መሆኑን ጉባዔው ገልጿል፡፡ በመሆኑም የንግድ ምልክት ምዝገባና ጥበቃ ሕጎች ስለንግድ ምልክት መመሳሰል ግልጽ ምላሽ ከሌላቸው፣ የልማት ፍላጎትና የአልሚዎች ቁጥር ባልተጣጣመበት ዓለም ውስጥ ያለውን አገራዊ የመልማት ፍላጎት ማሳካት እንደማይቻል አብራርቷል፡፡ ለኢንቨስትመንት ሰፊ በር የሚከፍት ትርጉም መስጠቱ ይበልጥ ሕገ መንግሥታዊነትን የሚያረጋግጥ ሆኖ እያለ፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሕጉን በጠባቡ የተረጎመበት አግባብ ሕገ መንግሥቱን እንደሚቃረን ገልጾ ጉባዔው አስተያየት መስጠቱ ታውቋል፡፡ በመሆኑም ለ“CROWN HOTEL” የወሰነው ውሳኔ  የሕገ መንግሥት ትርጉም እንደሚያስፈልገው በመግለጽ፣ መጋቢት 28 ቀን 2009 ዓ.ም. ድምዳሜ ላይ በመድረስ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም እንዲሰጥበት ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጉባዔው አስተያየቱን አቅርቧል፡፡ ", "passage_id": "510b7f82045895fcbaabc6a70d5e3919" }, { "passage": "የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ የሥራ አስፈፃሚ አካላትና የምርጫ ኮሚሽን ምርጫን በሚመለከት ያወጣው የምርጫ አዋጅ፣ ያሳለፏቸው ውሣኔዎችና የፈፀሟቸው ተግባራት “ከህገመንግሥቱ ጋር የሚቃረኑ” መሆናቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ በየነ።በዚህም መሠረት “በህገመንግሥቱ አንቀፅ 9 ንዑስ አንቀፅ 1 መሠረት እንዳልተደረጉ የሚቆጠሩ፣ የማይፀኑና ተፈፃሚነት የሌላቸው ናቸው” ሲል በሙሉ ድምፅ መወሰኑ ተገልጿል።በዚሁ በዛሬው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሣኔዎች ላይ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ቃል አቀባይ ወ/ሮ ሊያ ካሣ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ውሣኔው “ምክር ቤቱ በትግራይ ህዝብ ላይ ያለውን የመረረ ጥላቻ ያሳየ ነው” ብለዋል።ከአዲስ አበባና ከመቀሌ የተጠናቀሩትን ዘገባዎች ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።\n", "passage_id": "ae9a6826b6ad76a286f46c1fc581ce64" } ]
378cbd6960e8e53ca8d4ab0f4d86f220
80a6e8146b71e17ae9306e124d09ff45
የቀድሞ መንግሥት ባለሥልጣናት በአመክሮ ተለቀቁ
ዳግማዊት ግርማ አዲስ አበባ፡- የቀድሞ መንግሥት ባለስልጣናት ሌፍተናንት ጄኔራል አዲስ ተድላ እና ኮሎኔል ብርሃኑ ባየህ በአመክሮ መለቀቃቸውን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ገለጸ። በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የሙስናና የተደራጁ ወንጀል ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ፍቃዱ ፀጋ ትናንት በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ የቀድሞ መንግሥት ባለሥልጣናት የፍርድ ሂደታቸው በሌሉበት የታየ እና የጥፋተኝነት ውሳኔ ተላልፎባቸው የሞት ቅጣት ተጥሎባቸው ነበር። የጣልያን ኤምባሲ የቀድሞው ደርግ ባለስልጣናት የነበሩት ሰዎች በተመለከተ በሰጠው ኦፊሴላዊ ገለጻ ግለሰቦቹ ለረጅም ዘመናት ነፃነታቸው ተገድቦ የቆዩ ከመሆናቸው በተጨማሪ ከኤምባሲው ምንም አይነት ድጋፍ አይደረግላቸውም ነበር።በመሆኑም ከቤተሰቦቻቸው በሚላክላቸው ቀለብ በአንድ ቅጥር ግቢ በተወሰነ ስፍራ ብቻ ተወስነው ከእድሜ መግፋት እና ከተፈጥሮ ህመም ጋር በተገናኘም ተገቢውን ህክምና ለማግኘት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው መቆየታቸውን ኤምባሲው ማረጋገጡን ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ገልፀዋል።የእርቀ ሰላም ኮሚሽንም ግለሰቦቹ በሕግ አግባብ ተለቀው ቤተሰቦቻቸውን እንዲቀላቀሉ ለመንግስት ምክረ ሃሳብ ማቅረቡን ያስታወሱት ምክትል ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ፤ በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ክስ ተመስርቶባቸው በእስር ላይ ቆይተው የነበሩ የቀድሞው ደርግ አመራሮችም ከ10 ዓመታት በፊት ከእስር ወጥተው ከማህበረሰቡ ጋር እንዲኖሩ መደረጉን ገልጸዋል።በተቃራኒው በጣሊያን ኤምባሲ ውስጥ ተወስነው ለ30 ዓመታት የቆዩት እነኚህ ሰዎች ከመደበኛው የእርምት ስፍራ ባልተናነሰ በተወሰነ አነስተኛ ቅጥር ግቢ ውስጥ ወደ ህክምና ተቋማት እንኳን መውጣት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ከመንግስትም ሆነ ከቆዩበት የኤምባሲ ቅጥር ግቢ አስተዳዳሪ ምንም አይነት እንክብካቤ እና ድጋፍ ሳያገኙ መቆየታቸው በእስር ቢቆዩ ኖሮ ከሚፈጠርባቸው የመብት ገደብ አንጻር ቢበዛ እንጂ የሚያንስ እንዳልሆነ ግንዛቤ መወሰዱን አመልክተዋል።በመሆኑም መንግስት ከዚህም በላይ እነኚህን ሰዎች ከዚህ በኋላ ነጻነታቸውን ገድቦ ማቆየት የፍትህ አላማን ከማሳካትም አንጻር የሚጨምረው ውጤት የማይኖር በመሆኑ፣ ከፍርደኞቹ እድሜ እና የጤና ሁኔታ አንጻር የሰብዓዊነት እይታን ከግምት በማስገባት በግለሰቦቹ ላይ ተወስኖ የነበረውን የሞት ፍርድ ወደ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንዲቀየር ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሃሳብ ማቅረቡን ጠቁመዋል። በዚሁ ሃሳብ መሰረት ፕሬዚዳንቷ ቅጣቱ ወደ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት ሕገ-መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት እንዲለወጥ መወሰናቸውን በመግለጽ፤ በዚህም መሰረት መንግስት ግለሰቦቹ ካሉበት ስፍራ መውጣት ስለሚችሉበት ሁኔታ ከሕግ ማዕቀፍ እይታ አንጻር አስፈላጊውን ጥናት አድርጎ ግለሰቦቹ እስካሁን በኤምባሲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ነጻነታቸው ተገድቦ መቆየቱ አስተማሪነት ያለው መሆኑ ከግምት ገብቶ በአመክሮ እንዲለቀቁ አቤቱታ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም የቀረበውን አቤቱታ ተቀብሎ ግለሰቦቹ በአመክሮ እንዲለቀቁ መወሰኑን አስረድተዋል።የመንግስት ስርዓት ለውጡን ተከትሎ በጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ መንግስት በኃላፊነት ላይ የነበሩ እና በወቅቱ ተፈጽሞ በነበረ ወንጀል ተጠርጥረው እና ክስ ተመስርቶባቸው ከነበሩት አመራሮች እና የደርግ አባላት የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች ቀደም ብለው በአዲስ አበባ ከተማ ወደሚገኘው የጣሊያን ኤምባሲ ገብተው በዚያው ለ30 ዓመታት መቆየታቸው ይታወሳል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38061
[ { "passage": "ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከኢሕአዴግ ሊቀመንበርነትና ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ለመልቀቅ ጥያቄ ማቅረባቸውን አስታወቁ፡፡ ጥያቄያቸው ተቀባይነት እንደሚያገኝም እምነታቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ነገር ግን መልቀቂያቸው በኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴና በደኢሕዴን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ተቀባይነት ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ ከሥልጣን የሚለቁበትን ምክንያት ሲያስረዱ፣ አገሪቱ ያለችበት ሁኔታ አሳሳቤ ስለሆነ ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር ለማድረግ እንዲረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ወደፊትም በፓርቲያቸው ውስጥ ሆነው የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ አክለዋል፡፡", "passage_id": "1fd9d25ab0d24d80c6716f83f4894e4a" }, { "passage": "ከአራት ዓመታት በፊት በግንቦት ወር 2005 ዓ.ም. የታክስና ግብር ሕግ ጥሰትና የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው ክስ ተመሥርቶባቸው ሲከራከሩ የከረሙት የኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ባለቤት አቶ ስማቸው ከበደ፣ ሐሙስ ሐምሌ 6 ቀን 2009 ዓ.ም. ከእስር ተፈቱ፡፡አቶ ስማቸው ከተከሰሱበት የሙስና ወንጀል በነፃ የተሰናበቱ ቢሆንም፣ ከታክስና ግብር ጋር በተገናኝ በተመሠረተባቸው ክስ ጥፋተኛ ተብለው የእስራትና የገንዘብ ቅጣት ተወስኖባቸው ነበር፡፡ በዋና ሥራ አስኪያጅነት የሚመሩት ሲኤች ሲሜክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በ100,000 ብር ሲቀጣ፣ አቶ ስማቸው ደግሞ በስድስት ዓመታት እሥራት ተቀጥተዋል፡፡የእስር ጊዜያቸውን በመልካም ፀባይ ማሳለፋቸውን  በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ስለተረጋገጠ፣ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ተሰጥቶ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ትዕዛዝ ወዲያው ተግባራዊ ያላደረገው የማረሚያ ቤት አስተዳደር፣ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ተደርጎ ተጠይቋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ፍርደኛውን ያልለቀቀው ትዕዛዙን ባለማክበር ሳይሆን፣ አቶ ስማቸው ነፃ በተባሉበት የሙስና ወንጀል ዓቃቤ ሕግ ይግባኝ በማለቱ  ጉዳዩ እስከ ሰበር ደርሶ ያስቀርባል በመባሉ መሆኑን አስረድቷል፡፡ሰበር ሰሚ ችሎቱም ሆነ ይግባኙን እየመረመረው የሚገኘው ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ይግባኝ ሰሚ ችሎቱ ፍርደኛው ከእስር እንዳይፈቱ የሚል ትዕዛዝ ባለመስጠታቸውን በድጋሚ እንዲፈቱ ትዕዛዝ በመስጠቱ አቶ ስማቸው ከእስር ተለቀዋል፡፡ ", "passage_id": "66326250b7596e5cfe53c57351a9ccc7" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ፐሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ታስረው በዋስ ተፈቱ፡፡ አቶ ካሳሁን ለእስር የተዳረጉት  ፍርድ ቤት በሚመሩት ተቋም ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ እንዲፈጽሙ በተደጋጋሚ ሲጠየቁ ሊፈጽሙ ባለመቻላቸው፣ የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ አንደኛ አፈጻጸም ችሎት ትዕዛዝ በመስጠቱ መሆኑ ታውቋል፡፡አቶ ካሳሁን የታሰሩት በሥራ ክርክር ምክንያት እንደሆነ ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ውስጥ ከሰኔ 2006 ዓ.ም. ጀምሮ በክትትልና ግምገማ ባለሙያነትና በሲኒየር ማኅበራዊ ጉዳይ ኤክስፐርትነት ተቀጥረው ይሠሩ የነበሩት አቶ ሲሳይ ለሞምሳ የተባሉ ግለሰብ፣ ሕገወጥ በሆነ መንገድ ከሥራ መሰናበታቸውን ገልጸው በመሠረቱት ክስ ነው፡፡ ግለሰቡ ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት የክስ አቤቱታ እንዳስረዱት፣ በኢሠማኮ የክትትልና ግምገማ ባለሙያ ሆነው በሰኔ ወር 2006 ዓ.ም. ተቀጥረዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላ ደግሞ ከነሐሴ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ደመወዛቸው እንዲያድግ ከተደረገ በኋላ የሥራ ኃላፊነታቸውም ሲኒየር የማኅበራዊ ጉዳይ ኤክስፐርት መደረጋቸው ተገልጾ ደብዳቤ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ሠራተኛውና ተቋሙ በሰላም እየሠሩ ለሦስት ዓመታት እንደቆዩ፣ መስከረም 30 ቀን 2010 ዓ.ም. በተጻፈ ደብዳቤ የሥራ ውላቸው መቋረጡን እንደተነገራቸው በክስ ማመልከቻቸው ላይ ገልጸዋል፡፡ ከሦስት ዓመት በላይ በቋሚነት ሲያገለግሉ ቆይተውና ሥራውም ቀጣይነት እያለው እንደ ጊዜያዊ ሠራተኛ ‹‹ውሉ አልቋል›› ተብለው ከሥራ መሰናበታቸው ሕገወጥ መሆኑን በመግለጽ፣ ስንብቱ ‹‹ሕገወጥ ነው›› ተብሎ የካሳ፣ የማስጠንቀቂያ ጊዜ፣ የስንብት ክፍያና በተቋሙ ውስጥ ሊከፈላቸው ይገባ የነበረ የጉርሻ ክፍያ እንዲፈጸምላቸው እንዲወሰንላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀው ነበር፡፡ ተከሳሹ ኢሠማኮ (አቶ ካሳሁን) ለቀረበባቸው የክስ አቤቱታ በሰጡት ምላሽ እንዳስረዱት፣ ከሳሽ የተቀጠሩት በሰኔ ወር 2006 ዓ.ም. ሳይሆን ነሐሴ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ነው፡፡ ከሳሽ የሥራ ውላቸው ሲቋረጥ መቋረጡን ተቃውመው አቤቱታቸውን ለአቶ ካሳሁን ማስገባታቸውን አረጋግጠው፣ ምላሽ ሳይሰጧቸው ግን ለሌላ ሥራ ወደ ክልል እንደላኳቸው የክስ አቤቱታው ያስረዳል፡፡ ባለሙያው በተላኩበት የመስክ ሥራ መሰናበታቸው ተገቢ መሆኑ ተነግሯቸው እንደ አዲስ ሥራ እንዲቀጥሉ ሲነገራቸው፣ አለመስማማታቸውን አቶ ካሳሁን ለፍርድ ቤቱ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ከሳሽ የስንብት ደብዳቤያቸውን አልቀበልም ብለው ሥራቸውን የቀጠሉ ቢሆንም፣ የውል ጊዜያቸው ማለቁን ተከትሎ ስንብቱ መከናወኑ ተገቢ መሆኑንና ሊከፈላቸው የሚገባ ክፍያ እንደሌለ በመግለጽ፣ ምላሻቸውን መስጠታቸውን የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ይገልጻል፡፡ፍርድ ቤቱ የተለያዩ ጭብጦችን ይዞ ክርክሩን መመርመሩን፣ ምስክሮችንም ከሰማ በኋላም ሰበር ሰሚ ችሎች በመዝገብ ቁጥር 25526 የሰጠውን አስገዳጅ ትርጉም በማየት የመጨረሻ ፍርድ ሰጥቷል፡፡ ኢሠማኮ በከሳሽ ላይ የወሰደው ዕርምጃ ተገቢ አለመሆኑንና የቀረበበትን ክስ ማስተባበል አለመቻሉን በመግለጽ፣ ከሳሽ ላቀረቡት ክስ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ በመሆኑም ኢሠማኮ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 43(4ሀ) መሠረት 46,008 ብር የካሳ ክፍያ፣ በአንቀጽ 35(1ለ) እና 43(4ሀ) መሠረት የሁለት ወር ደመወዝ 15,336 ብርና በአንቀጽ 40(1 እና 2) መሠረት የስንብት ክፍያ 10,539 ብር፣ በልዩነት ሳይከፈላቸው የቀረ 7,486 ብርና ለደረሰባቸው የመጉላላት ኪሳራ 2,000 ብር በድምሩ 81,369 ብር እንዲከፍል ውሳኔ ሰጥቶ ነበር፡፡ነገር ግን ተቋሙ እንደ ፍርዱ ሊፈጽም ባለመቻሉ ፕሬዚዳንቱ አቶ ካሳሁንን ፎሎ በፖሊስ ታስረው ጥቅምት 13 ቀን 2011 ዓ.ም. ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ የተሰጠ ቢሆንም ተበዳይ ግን፣ ‹‹ከአገር ወጥተው ላይመለሱ ይችላሉ›› የሚል ሥጋት ለፖሊስ በማመልከታቸው፣ ፖሊስ አቶ ካሳሁንን መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር አውሎ፣ በተቋሙ የውጭ ግንኙነትና ሕዝብ ግንኙነት መምርያ ኃላፊ አቶ መአሹ በሪሁ ዋስትና መፈታታቸው ታውቋል፡፡ ", "passage_id": "7278dced665937046db40065a5afab2d" }, { "passage": "አቶ እንዷለም ከአንድነት ለፍትህ እና ዲሞክራሲ ፓርቲ መስራቾች መካከል አንደኛው ሲሆኑ መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም ከታሰሩ በኋላ ለሽብር ጋር በተያያዘ በተመሰረተባቸው ክስ የዕድሜ ልክ እስራት እንደተፈረደባቸው ይታወቃል።\n\nእስክንድር በእስር ላይ ሳለ እ.ኤ.አ የ2012ን የፔን/ባርባራ ጎልድስሚዝ የፅሁፍ ነፃነት እና እ.ኤ.አ የ2017 የዓለም አቀፍ የፕሬስ ተቋምን የዓለም የፕሬስ ነፃነት የጀግንነት ሽልማትን ተቀዳጅቷል።\n\n ሁለቱም የተከሰሱባቸውን ወንጀሎች የሚያስተባብሉ ሲሆን የተለያዩ የዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋቾች እስራታቸውን በፖለቲካ የተነሳሳ ነው በማለት ሲያጣጥሉት ቆይተዋል።\n\n የፋና ዘገባ እንደሚለው ከሆነ ከፌዴራል እስር ቤቶች በይቅርታ ከሚወጡ ታራሚዎች በተጨማሪ ከአማራ ክልል እሴ ቤቶች ለሚገኙ 119 ታራሚዎች ይቅርታ ተደርጓል። \n\nዘገባው ጨምሮ ታሳሪዎቹ የሚፈቱት በይቅርታ ቦርድ ለፕሬዚዳንቱ ከቀረበ፣ የተሃድሶ ስልጠናም ከወሰደ በኋላ ብሏል። \n\nየጥፋተኝነት ፍርድ ከተላለፈባቸው እና የእስር ቅጣታቸውን በመፈፀም ላይ ከሚገኙት ውጭ ክሳቸው በመታየት ላይ ያለ 329 ተጠርጣሪዎች ክሳቸው ተቋርጦ እንዲፈቱ ይደረጋልም ተብሏል።\n\n ", "passage_id": "3ab97e5e63f6e0c3092f526801bc24df" }, { "passage": "ሌሎች ተጠርጣሪዎችም እንደሚፈቱ ተገለጸፍርደኞችን በሚመለከት የፕሬዚዳንቱ ውሳኔ አልታወቀም የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ከየካቲት 1 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ክሳቸው እንዲቋረጥ ያደረገላቸው አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ ሰባት ተጠርጣሪዎች፣ ማክሰኞ የካቲት 6 ቀን 2010 ዓ.ም. ከእስር ተለቀቁ፡፡ በተጨማሪም ከ340 በላይ ተጠርጣሪዎች ረቡዕ የካቲት 7 ቀን 2010 ዓ.ም. እንደሚፈቱ ታውቋል፡፡ተጠርጣሪዎቹ ከየካቲት 5 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ የተሃድሶ ትምህርት ወደሚወስዱበት ኦሮሚያ ክልል ሰንዳፋ ፖሊስ ማሠልጠኛ ተቋም መወሰዳቸው ተገልጿል፡፡ ቀደም ብለው ከተፈቱት በተጨማሪ ከየካቲት 1 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ክሳቸው እየተቋረጠ የሚገኙ ተጠርጣሪዎች የተሃድሶ ትምህርት እየወሰዱ መሆኑ ታውቋል፡፡ሰኞ የካቲት 5 ቀን 2010 ዓ.ም. የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ፣ የወጣቶች ሊግ ሊቀመንበር አቶ ጉርሜሳ አያና፣ አቶ ደጀኔ ጣፋና አቶ አዲሱ ቡላም ክሳቸው ተቋርጧል፡፡ ነገር ግን አራቱም ተጠርጣሪዎች ለሁለት ጊዜያት ችሎት በመድፈር ወንጀል ጥፋተኛ በመባላቸው ስድስት፣ ስድስት ወራት በድምሩ ለአንድ ዓመት የእስራት ቅጣት ስለተወሰነባቸው፣ ከእስር የሚፈቱት ለፌዴራል ይቅርታ ቦርድ ቀርቦ ውሳኔ ሲሰጥና የአገሪቱ ርዕሰ ብሔርን ይሁንታ ሲያገኝ ብቻ ነው፡፡ የፍርድ መዝገቡ ለይቅርታ ቦርድ የካቲት 5 ቀን 2010 ዓ.ም. ተልኮ የፕሬዚዳንቱን ይሁንታ በማግኘቱ፣ ማክሰኞ የካቲት 6 ቀን 2010 ዓ.ም. ከእስር ተለቀዋል፡፡ በአቶ ጉርሜሳ አያና መዝገብ ተካተው የነበሩት የአቶ ጌቱ ጋሩማ፣ የአቶ ተስፋዬ ሊበንና የአቶ በየነ ሩዳ ክስም በመቋረጡ እነሱም ተለቀዋል፡፡በሌላ የክስ መዝገብ ተከሰው የነበሩት የቀድሞ መኢአድ አመራር የነበሩት አቶ ማሙሸት አማረም ክስ ተቋርጦ ወደ ተሃድሶ መግባታቸው ታውቋል፡፡ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ሌሎች የክስ መዝገቦችን እያጣራ የተጠርጣሪዎችን ክስ በማቋረጥ ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በማጣራት ለፌዴራል ይቅርታ ቦርድ የስም ዝርዝራቸው ከቀረቡት ውስጥ፣ የአንድነት ለፍትሕና ዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) አመራር የነበረው አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ (14 ዓመታት ተፈርዶበት ነበር) እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ 413 ፍርደኞች የቦርዱን ውሳኔ አግኝተው ለርዕሰ ብሔሩ ዝርዝራቸው መላኩ የተሰማ ቢሆንም፣ ፕሬዚዳንቱ የሰጡት ውሳኔ አልታወቀም፡፡ ሪፖርተር የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤትን ለማነጋገር ጥረት ያደረገ ቢሆንም አልተሳካም፡፡ ", "passage_id": "b06a69594b6321b3639eb7133fc8d82c" } ]
bfd6b7f4d45351227cefe11590efa6df
d1c9aef43a71a21f6f2fa1a69b92f7ea
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አዲስ የካቢኔ አባላትን ይፋ አደረገ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- በትግራይ ክልል አዲስ የካቢኔ አባላት ተሹመው ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ። እንደ ኢዜአ ዘገባ፣ የአስተዳደሩ የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ካሣ በክልሉ ከሚያስፈልጉ 16 የካቢኔ አባላት መካከል 11 ተሿሚዎች በይፋ ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።በዚሁ መሠረት፡- ዶክተር ካህሣይ ብርሃኑ …… የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊኢንጂነር አሉላ ሃብተአብ …… የኮንስትራክሽን፣ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊዶክተር ፋሲካ አምደ ስላሴ …… የጤና ቢሮ ኃላፊአቶ አበራ ንጉሴ ………. የፍትህ ቢሮ ኃላፊወይዘሮ እቴነሽ ንጉሴ ……… የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊአቶ ዮሴፍ ተስፋይ ………. የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ተስፋይ ሰለሞን …….. የትምህርት ቢሮ ኃላፊዶክተር ገብረህይወት ለገሠ ……. የውሃ ጥናትና ዲዛይን ቢሮ ኃላፊአቶ ሰለሞን አበራ …….. የውሃ ሃብት ቢሮ ኃላፊአቶ አብርሃ ደስታ ……. የማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እና አቶ ገብረመስቀል ካሣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ተገልጿል።ሌሎች ያልተሟሉ የካቢኔ አባላት በቀጣዮቹ ሳምንታት ተሟልተው ወደ ስራ ይገባሉአዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38069
[ { "passage": "ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተለያዩ ሹመቶችን መስጠታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ገልጿል። የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በትናንትናው እለት ስብሰባ አድርጎ የተለያዩ ዉሳኔዎችን ካሳለፈ በኋላ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሱን ሹመታቸውን ይፋ ያደረጉት፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ አስር ሹመቶችን የሰጡ ሲሆን በቅርቡ ከብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት በታገዱት አቶ ለማ መገርሳ ቦታ ዶ/ር ቀንዓ ያደታ የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው ተሾመዋል፡፡\nአቶ ለማ መገርሳ በስራ ቦታቸው ላይ እንዲሁም በፓርቲው ስብሰባዎች እንደማይገኙ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው መታገዳቸውን ተከትሎ ፓርቲው መግለጹ ይታወቃል፡፡\nየመከላከያ ሚኒስትር ሆነው የተሸሙት ዶ/ር ቀንዓ ያደታ የሕገ መንግስት አጣሪ ጉባኤ አባል ሆነው በማገልገል ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡ ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሰላም እና ደህንነት (Peace and Security) ፒኤችዲ ያላቸው ዶ/ር ቀንዓ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የሹመት ቦታዎች አገልግለዋል፡፡ ካገለገሉባቸው ኃላፊነቶች መካከል የሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ፣ የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ፣ የኦሮምያ አስተዳደር ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ፣ የጅማ ዞን ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፣ የጉምሩክ ኃላፊ እና የሰንዳፋ ፖ/ኮሌጅ ዲን ሆነው ያገለገሉበት ይገኙበታል፡፡\nበቅርቡ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሆነው የተሾሙት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከኃላፊነታቸው ተነስተው በምትካቸው ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቴዎስ ተሾመዋል፡፡ ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቴዎስ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ነበሩ፡፡\nየማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ሳሙኤል ሁርካቶ በፕሮፌሰር ኂሩት ወልደ ማርያም ምትክ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ሆነዋል፡፡ በእርሳቸው ቦታ ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ የነበሩት ኢንጂነር ታከለ ኡማ የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ሆነው እንዲያገለግሉ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሾመዋል፡፡\nአቶ ተስፋዬ ዳባ እና አቶ ፍቃዱ ጸጋ ደግሞ ምክትል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ እንዲሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሹመት ሰጥተዋቸዋል፡፡ከዚህ ቀደም የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር እንዲሆኑ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሰጣቸውን ሹመት አልቀበልም በማለት ተንሳፈው የቆዩት አቶ ዮሐንስ ቧያለው አሁን የኢትዮጵያ የውጭ ግነኙነት ስትራቴጂክ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር እንዲሆኑ አዲስ ሹመት ተሰጥቷቸዋል፡፡ አቶ ዮሐንስ ቧያለው በሕይወት በሌሉት በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ስም የተሰየመን ተቋም የማገልገል ፍላጎት የሌላቸው መሆኑ የቀድሞውን ሹመት ላለመቀበላቸው ምክንያት መሆኑን በወቅቱ ለአል ዐይን ገልጸው ነበር፡፡\nየጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ የነበሩት አቶ ንጉሡ ጥላሁን የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን ዛሬ አዲስ ሹመት አግኝተዋል፡፡\nአቶ እንደአወቅ አብቴ ከአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባነታቸው ተነስተው የብረታ ብረት ኢንጅኔሪንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነዋል፡፡\nየሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር የነበሩት ፕሮፌሰር ኂሩት ወልደ ማርያም በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሆነው ተሹመዋል፡፡ ፕሮፌሰር ኂሩት በቅርቡ ከአቶ ለማ መገርሳ እና ዶ/ር ሚልኬሳ ሚደጋ ጋር ከብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት የታገዱትን የወ/ር ጠይባ ሀሰንን ቦታ ነው የተኩት፡፡\nበኢትዮጵያ ህግ መሰረት ሹመቱ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ቀርቦ ሲጸድቅ የሚጸና ይሆናል፡፡", "passage_id": "6ef8e0152c8b00ddb7a1f0d87130c027" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥር 20 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት የተለያዩ የስራ ሃላፊዎችን ሹመት አፀደቀ።ሹመቱን ምክር ቤቱ እያካሄደ ባለው 5ኛ የስራ ዘመን 18ኛ መደበኛ ጉባኤው ነው ያጸደቀው።በዚህ መሰረት ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የፍትህና መልካም አስተዳደር ክላስተር ሃላፊ ሆነው ተሾመዋል።ከዚህ ባለፈም ዶክተር ሰለሞን ኪዳነ በቢሮ ሃላፊ ማዕረግ የትግራይ ከተሞች ክትትል ሃላፊ ሆነው መሾማቸውን ከህውሓት የፌስ ቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በተጨማሪም ምክር ቤቱ የአቶ አስመላሽ ወልደስላሴ የትግራይ ክልል በይነ መንግስታት ጽህፈት ቤት ሃላፊነት ሹመትም አጽድቋል። ", "passage_id": "a990c6316f04f285b926ab8a12eaa941" }, { "passage": " አዲስ በቀረበው የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው ረቂቅ አዋጅ መሰረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ እጩ የካቢኔ አባላትን ለሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው ያስፀድቃሉ።የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው እለት እያካሄደ ባለው 2ኛ መደበኛ ስብሰባው የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።በረቂቅ አዋጁ መሰረትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ 19ኙን የሚኒስትር መስሪያ ቤቶች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው እንደሚያፀድቁ ይጠበቃል።በዚህም መሰረት፦ \n1. የሰላም ሚኒስቴር\n2. የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር\n3. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር \n4. የገንዘብ ሚኒስቴር\n5. ጠቅላይ አቃቤ ህግ \n6. የግብርና ሚኒስቴር \n7. የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር\n8. የገቢዎች ሚኒስቴር\n9. የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር\n10. የትራንስፖርት ሚኒስቴር\n11. የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር\n12. የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር\n13. የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር\n14. የትምህርት ሚኒስቴር\n15. የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር\n16. የጤና ሚኒስቴር\n17. የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር\n18. ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር \n19. የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴርበረቂቅ አዋጁ መሰረት ከአሁን በፊት የነበሩ እና ከዚህ በኋላ የማይቀጥሉ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች\n1. የፌደራል ጉዳዮችና አርብቶ አደር ሚኒስቴር – በሰላም ሚኒስቴር ስር የተጠቃለለ\n2. የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት – በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት የፕሬስ ሰክሬታሪያት የሚተካ\n3. የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር – የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር የተጠቃለሉ\n4. የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር- በአንድ ላይ የተዋሃዱ\n5. የከተማ እና ቤቶች ልማት ሚኒስቴር – ከኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ጋር የተዋሃዱምክር ቤቱ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።በማብራሪያቸውም መንግስት ባለፉት ጥቂት ወራት ሲሰራው በነበረው የማሻሻያ ስራ ሰላምን ማረጋገጥ፣ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖር፣ ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲጠበቁ፣ ህገ መንግስቱ እና የህግ የበላይነት እንዲከበር እና ከሌብነት የፀዳ አሰራር እንዲኖር የህዝቡ ፍላጎት መሆኑን ተረድተናል ብለዋል።ለዚህም ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ የመንግስት ተቋማትን በአዲስ መልክ እንዲደራጁ እንዲሁም ፈጣን ምላሽ በሚሰጥ መልኩ የካቢኔ አባላትን ቁጥር ወደ 20 ዝቅ እንዲል መወሰኑን አንስተዋል።ረቂቅ አዋጁ የአስፈፃሚ አካላትን ማጠናከር የሚችል መሆኑንም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ያስረዱት።በቀጣይም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ፍርድ ቤቶች፣ የዴሞክራሲ ተቋማት፣ የምርጫ ቦርድ፣ የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም እና ሌሎች ተቋማትም ራሳቸውን በመፈተሽ እንደ አዲስ እንደሚደራጁ አስረድተዋል። ", "passage_id": "1f388e3b474e6cdf014fa50ac96f369a" }, { "passage": "የክልሉ ምክር ቤት 5ኛ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችንና ተጨማሪ በጀት በማጽደቅ ዛሬ አጠናቋል።ምክር ቤቱ አቶ አማኑኤል አሰፋ- የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ፣አቶ ነጋ አሰፋ- የክልሉ የወጣቶች ጉዳይና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ እና አቶ ረዳኢ ሃለፎም የህዝብና መንግስት ግንኙነት ቢሮ ሃላፊ አድርጎ ሾሟል ።ምክር ቤቱ ከዚህ ባለፈም የዶክተር አትንኩት መዝገቡን ለክልሉ ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ሃላፊነት እውቅና ሰጥቷል ።የትግራይ ክልል ምክር ቤት በተለያዩ ቦታዎች የሚሰሩ የ38 ዳኞችን ሹመትና  ከ574 ሚሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት በማጽደቅ ጉባዔውን አጠናቋል።", "passage_id": "c9227790daf4009ef9fd5ccde267f37e" }, { "passage": "የአረና ትግራይ ለዴሞክራሲና ሉአላዊነት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አብርሃ ደስታ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ዋና ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ፡፡\nለ13 ዓመታት የአረና ሊቀመንበር ሆነው የቆዩት አቶ አብርሃ በዶ/ር ሙሉ ነጋ በሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ነው በኃላፊነት የተመደቡት፡፡ የብልጽግና ፓርቲ አቶ አብርሃን “ለነፃነት የታገለ ወጣት ሲሆን በርካታ ጊዜያትንም በእስር አሳልፏል” ሲል ገልጿቸዋል፡፡\nአቶ አብርሃ ደስታ በመቐለ ዩንቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህር የነበሩ ሲሆን በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ አስተያየት በመስጠት ይታወቃል፡፡\nበተመሳሳይ ዜና አቶ አታክልቲ ኃይለስላሴ የከተማዋ ከተማ ከንቲባ በመሆን መሾማቸው የሚታወስ ሲሆን የከተማዋን ነዋሪዎች የልማትና የጸጥታ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ገልጸዋል፡፡\nየጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሙሉ ነጋ (ዶ/ር) በትግራይ እየተዋቀረ ያለው ጊዜያዊ የመንግስት አስተዳደር ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ኣካቶ እንደሚመሰረት መግለጻቸው ይታወሳል፡፡\nበዚህም መሰረት አረና፣ ትዴፓ እና አሲምባን የመሳሰሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በክልሉ ካቢኔ ውስጥ እንዲገቡ እየተደረገ ሲሆን ከዚህ በፊት በነበረው የክልሉ ነበራዊ ሁኔታ እነዚህ አካላት በፖለቲካ አመለካከታቸው የተነሳ ሲታሰሩ፣ ሲገደሉና ሲሳደዱ ስለመቆየታቸው ተገልጿል፡፡\nየክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ከሰኞ ታህሣሥ 5 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ስራ የገባ ሲሆን ትናንት ማክሰኞ ዕለት የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሙሉ ነጋ (ዶ/ር) በመቐለ ከተማ የመንግሥት ሰራተኞችን አወያይተዋል፡፡ በከተማዋ የመንግሥት ስራዎች በመጀመር ላይ ሲሆኑ ሁለት ክፍለ ከተሞች ሙሉ በሙሉ ስራ መጀመራቸውንም ዶ/ር ሙሉ ገልጸዋል፡፡\n", "passage_id": "1908be74f36bc07fd4f5e02217e5a8e0" } ]
909f92a2160e2c657fe5c05eb44ed711
313ede6ff644dcd62e4bc6d3b3c742de
በመተከል እየተፈጸመ ያለው ግድያ በክልሉ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እጅጉን መዳከሙን እንደሚያሳይ ኢሰመኮ ተናገረ
 በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እየተበራከተ የመጣው እና ከሰሞኑ ሌሊት ላይ የታጠቁ ኃይሎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩ ነዋሪዎች ላይ በለኮሱት እሳት እና በተኩስ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን የሚያሳይ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ። ኮሚሽኑ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ መሆኑንም ተናግሯል።ኮሚሽኑ ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፤ ታኅሣሥ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን፣ ቡለን ወረዳ፣ በኩጂ ቀበሌ ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ላይ የታጠቁ ኃይሎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩ ነዋሪዎች ላይ በለኮሱት እሳት እና በተኩስ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን ነው። በመሆኑም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ ነው።በመግለጫው እንደተመላከተው፤ ኢሰመኮ የጥቃቱን ሂደት በተመለከተ ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከሚመለከታቸው አካላት እና ከተጎጂዎች ጋር በመነጋገር ሲከታተልና ሲያጣራ ቆይቷል። በኩጂ ቀበሌ ከወረዳው መቀመጫ ከሆነችው ቡለን ከተማ 90 ኪ.ሜ. ርቃ የምትገኝ ሲሆን የሺናሻ፣ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች ይኖሩባታል። ለቀበሌው የተመደበ የፖሊስ ወይም የፀጥታ ኃይል አለመኖሩን ኮሚሽኑ በክትትሉ መሰረት ተረድቷል። ኮሚሽኑ ሁኔታውን እስካጣራበት ጊዜ ድረስ በቡለን ሆስፒታል 36 ተጎጂዎች እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን አብዛኞዎቹ በጥይት ሌሎቹ በቀስት የቆሰሉ መሆናቸውን ኢሰመኮ በምልከታ አረጋግጧል። በተጨማሪም ሰዎች ጥቃት የደረሰባቸውን ሁኔታ የሚያሳዩና የሚረብሹ የፎቶግራፍ ማስረጃዎች ለኮሚሽኑ ደርሰውታል። በሰው ሕይወት እና በአካል ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ የደረሱ ሰብሎችና የተሰበሰቡ ማሳዎች በእሳት ጋይተዋል። ቢያንስ 18 ያክል ነዶዎች ሲቃጠሉ ማየታቸውን አንድ ተጎጂ አስረድተዋል። በጨላንቆ እና ዶሼ ቀበሌዎች ቤቶች እየተቃጠሉ እንደሆነ ከአካባቢው ለኮሚሽኑ የተላኩ መረጃዎች ያመለክታሉ። በድባጤ ወረዳ ዶንበን ቀበሌ ስጋት የገባቸው ነዋሪዎች ከታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ቀዬአቸውን ጥለው እየተሰደዱ እንደሆነም ኮሚሽኑ ረድቷል። አካባቢውን በቅርበት እንዲጠብቅ የተመደበው ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊት ታኅሣሥ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ለማረጋጋት ተግባር ወደቦታው ተልከው የነበሩ አንድ የፌዴራል እና ሁለት የክልሉ አመራሮችን ለማጀብ በሚል አካባቢውን ለቅቆ መሄዱ ታውቋል።ጥቃቱ የጀመረው ይህንኑ ተከትሎ እንደሆነና ሌሊቱን የጀመረው ጥቃት እስከ ቀኑ አጋማሽ ድረስ መዝለቁንም ለማወቅ ተችሏል። ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው ተጎጂዎች እንደሚሉት በጥቃቱ ከሞቱ ሰዎች መካከል አብዛኛው የሺናሻ ተወላጆች ናቸው። ከዚህ ቀደም በነበሩ ጥቃቶች ፈጻሚዎቹ ከ”ጫካ” የሚመጡ ሰዎች የነበሩ ቢሆንም፣ በዚህኛው ጥቃት “በስምና በመልክ የሚያውቋቸው”የበኩጂ ቀበሌ ነዋሪዎች ጭምር መሳተፋቸውን ከጥቃቱ የተረፉ ተጎጂዎች ገልጸዋል። ኢሰመኮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚከሰቱ ጥቃቶችን ተደጋጋሚነትና የክልሉን ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ሁኔታ አስመልክቶ፣ የፌዴራሉንና የክልሉን መንግሥታት የተጠናከረ ትብብርና ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሻ ሲያሳስብ መቆየቱ ይታወሳል። ይሁንና ጥቃቶቹ በመልክ እና በስፋት እየተባባሱ መጥተዋል። ስለሆነም፣ በጥቃቱ ጉዳት ለደረሰባቸው እና ለተፈናቀሉ ሰዎች የህክምና እና ሰብዓዊ እርዳታ እንዲቀርብ፣ እንዲሁም ተገቢው ማጣራትና ጥቃቱን ባለመከላከልም ሆነ በሌላ መልኩ ጥቃቱን የፈጸሙና ያባባሱ ሰዎችን ሕግ ፊት የማቅረቡ ሂደት ከወዲሁ እንዲጀመር ኮሚሽኑ ያሳስባል። በአካባቢው የሚገኘውን የፀጥታ ኃይልና መዋቅር የሰዎችን ደኅንነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በከፍተኛ ደረጃ በአፋጣኝ እንዲጠናከር ኢሰመኮ ጥሪ አቅርቧል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38060
[ { "passage": "ሚሼል ባሽሌት\n\nበሚሼል ባሽሌት የሚመራው ኮሚሽኑ \"ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኩል የጋራ ምርመራ ለማካሄድ የቀረበለትን ጥያቄ ተቀብሎ ሰኞ ዕለት አውንታዊ መልስ ሰጥቷል\" ሲሉ ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን ቃል አቀባይ የሆኑት ጆናታን ፎውለር ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ተናግረዋል። \n\nበጥቅምት ወር ማብቂያ ላይ የተቀሰቀሰውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች በትግራይ ክልል ውስጥ ከባድ የሰብአዊ መብቶች ጥሰትና የንበረት ውድመት መፈጸሙን የሚገልጹ ሪፖርቶችን አውጥተዋል። \n\nየተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የሆኑት ሚሼል ባሽሌት ከሳምንት በፊት ባወጡት መግለጫ በትግራይ ግጭት የተሳተፉ አካላት \"የጦር እና በሰብአዊነት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች ፈጽመው ሊሆን እንደሚችል\" ገልጸው ነበር። \n\nሚሸል ባሽሌት \"የሚረብሹ\" ያሏቸው የመደፈር፣ የዘፈቀደ ግድያ፣ መጠነ ሰፊ የንብረት ውድመትና ዘረፋ መፈጸማቸውን የሚያመለክቱ ሪፖርቶች እየወጡ መሆኑን ጠቅሰው፤ ግልጽና ነፃ ምርመራ ካልተካሄደና ጥሰቱን የፈፀሙትን አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ ካልተቻለ እነዚህ ጥቃቶች ሊቀጥሉ እንደሚችሉ ስጋታቸውን ገልጸው ነበር።\n\nኮሚሽነሯ ከትግራይ የሚወጡ ተያያዢነት ያላቸውና ተአማኒ ያሏቸውን ሪፖርቶች ጠቅሰው በግጭቱ ውስጥ ተሳታፊ በሆኑ የተለያዩ ወገኖች የተፈፀሙ ከባድ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች እና የሰብአዊ እርዳታ ሕጎች ጥሰት መፈጸማቸውን እንደሚያመለክቱ ተናግረዋል። \n\nበዚህም የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በትግራይ ክልል ተፈጸሙ የተባሉትንና እንደ ጦር ወንጀል ሊቆጠሩ የሚችሉ ሪፖርት የተደረጉ የጅምላ ግድያዎችን፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችንና ወሲባዊ ጥቃቶችን ለመመርመር እንዲችል ፈቃድ እንዲሰጠው ጠይቆ ነበር። \n\nየመንግሥታቱ ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ በእነዚህ ድርጊቶች ውስጥ ሳይሳተፉ አይቀሩም በሚል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን፣ ህወሓትን፣ የኤርትራ ወታደሮችን፣ የአማራ ክልል ኃይሎችን ጠቅሶ ነበር። \n\nየኢትዮጵያ መንግሥትም ተፈጽመዋል ስለተባሉት የሰብአዊ መብት ጥሰቶችና ግድያዎችን በሚመለከት ከተለያዩ ወገኖች በኩል የሚወጡትን መረጃዎች መሠረት በማድረግ የአገሪቱን የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን፣ ዐቃቤ ሕግን፣ የትግራይ ገዜያዊ አስተዳደርንና የፌደራል ፖሊስን ያካተተ ቡድን አቋቁሞ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል። \n\nበተጨማሪም የአፍሪካ ሕብረትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት እየተደረገ ባለው ምርመራ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ በማድረግ ቀረቡትን ክሶች ለማጣራት ፈቃደኝነቱን አሳይቷል። \n\nጥቅምት 24/2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል በሚገኘው የሰሜን ዕዝ ላይ የህወሓት ኃይሎች የፈጸሙትን ጥቃት ተከትሎ በተቀሰቀሰው ጦርነት ሳቢያ የጠፋው ህይወት ምን ያህል እንደሆነ በትክክል የማይታወቅ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ ሳይሞቱ እንዳልቀሩ የእርዳታ ድርጅቶች ይገምታሉ። \n\nከዚህ በተጨማሪም ግጭቱን በመሸሽ ከ60 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች ድንበር ተሻግረው ወደ ሱዳን የገቡ ሲሆን በመቶ ሺህ የሚቆጠሩት ደግሞ እዚያው በክልሉ ውስጥ ተፈናቅለው እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑ ተገልጿል። \n\n ", "passage_id": "7cfa174b62fcd429ce6f3ca4821475c5" }, { "passage": "በማይካድራ ከተማ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ ቢያንስ 600 ሰዎች መገደላቸውንና ቁጥሩም ከዚህ እንደሚበልጥ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ።ኮሚሽኑ ይህንን የገለጸው በማይካድራ ከተማ የተከሰተውን ጥቃት ተከትሎ በከተማዋና በአካባቢው ባሉ ሌሎች ስፍራዎች ያካሄደውን ምርመራ ይፋ ባደረገበት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ ነው። ከሁለት ሳምንት በፊት በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ክፍል በምትገኘው የማይካድራ ከተማ የተፈጸመው ጥቃት በአካባቢው መስተዳድር የጸጥታ መዋቅርና 'ሳምሪ' በተባለ ኢ-መደበኛ የወጣቶች ቡድን መፈጸሙንም ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ አመልክቷል። በዚህም መሰረት የአካባቢው መስተዳድርና 'ሳምሪ' በተባለው ቡድን የተፈጸመው ጥቃት፤ ግድያ፣ ጉዳትና ውድመት፤ ጠቅላላ ድርጊቱና ውጤቱ \"ግፍና ጭካኔ የተሞላበት በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመ የጭፍጨፋ ወንጀል\" ነው ሲል ኮሚሽኑ ገልጾታል።ኮሚሽኑ ይህ ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት \"በሰብአዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል እና የጦር ወንጀል ሊሆን እንደሚችል\" ያመለከተ ሲሆን፤ ለዚህም ኢሰመኮ ዝርዝር ማስረጃዎቹን እና ወንጀሉን የሚያቋቁሙትን የሕግና የፍሬ ነገር ትንተና በሙሉ ሪፖርቱ ላይ በዝርዝር አጣርቶ የሚያቀርብ መሆኑን አሳውቋል።ይህ ድርጊት በማይካድራ የነበረው የሚሊሽያና የፖሊስ መዋቅር የፌዴራሉ ሠራዊትን እርምጃ ሸሽቶ አካባቢውን ለቆ ከመውጣቱ በፊት \"ሳምሪ ከተባለ መደበኛ ያልሆነ የትግራይ ወጣቶች ቡድን ጋር በመተባበር በተለይ \"አማሮችና ወልቃይቴዎች\" ያሏቸው በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት\" መፈጸማቸውን አመልክቷል። በዚህም ቡድኑ \"ከቤት ቤት እየዞሩና በየጐዳናው ላይ ያገኙትን ሰው በገመድ በማነቅ፣ በስለት፣ በመጥረቢያ፣ በዱላ በመደብደብ ገድለዋል፣ የአካል ጉዳት አድርሰዋል፣ እንዲሁም ንብረት አውድመዋል\" ሲል ኮሚሽኑ ገልጿል። ኮሚሽኑ ጨምሮም \"'ሳምሪ' የሚባለው የትግራይ ወጣቶች ቡድን በዚህ ከባድ ወንጀል ላይ ቢሰማራም፤ በአንጻሩ የትግራይ ብሔረሰብ ተወላጆች የሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች አጥቂው ቡድን ሲያሳድዳቸው የነበሩ ሰዎችን በቤታቸው፣ በቤተክርስቲያንና በእርሻ ቦታ ደብቀው እንዳተረፏቸው\" ኢሰመኮ ምስክሮችን ጠቅሶ በሪፖርቱ ላይ አስፍሯል። በተጨማሪም የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) \"በማይካድራ በአነስተኛ ጽንፈኛ ቡድን የተፈጸመው በማንነት ላይ የተመሰረተ እጅግ ዘግናኝ ወንጀል ልብ ሰባሪ ቢሆንም፤ በአንጻሩ ኢትዮጵያውያን በብሔር ሳይለያዩ አንዱ የሌላው ጠባቂ ሆነው መታየታቸው ልብ ይጠግናል\" በማለት ለወደፊቱ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ኮሚሽነሩ ጨምረውም በዚህ ጥቃት የተጎዱ ሰዎችንና አካባቢዎችን መልሶ ከማቋቋምና በተጨማሪ፤ \"በዚህ ከባድ ወንጀል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ የተሳተፉ በየደረጃው ያሉ ጥፋተኞችን በሕግ ፊት ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ ያስፈልጋል\" ብለዋል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም በማይካድራ ከተማ የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ያደረገውን ምርመራ በተመለከተ ያወጣው ባለስድስት ገጽ ዘገባ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት እንደሆነ አመልክቷል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ጥቃቱን የፈፀሙት የህወሓት ታጣቂዎች ናቸው ቢሉም የትግራይ ክልል ባለስልጣናት በበኩላቸው በግድያዎቹ እጃችን የለበትም በማለት ውድቅ አድርገውታል።የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ውንጀላው \"መሰረት\" የሌላው ነው በማለት፤ ጥቃቱ በገለልተኛ ወገን ይጣራ ማለታቸው የሚታወስ ነው።ከሳምንት በፊት ስለክስተቱ ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ አምነስቲ ኢንትርናሽናል በማይካድራ ስለተፈጸመው ጥቃት ተመሳሳይ ሪፖርት ማውጣቱ ይታወሳል። ክስተቱን ተከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኃላፊ ሚሼል ባችሌት በማይካድራ ከተማ ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል የሚለው ሪፖርት እንዲጣራ መጠየቃቸው የተዘገበ ሲሆን በተጨማሪም \"ግድያዎቹ መረጋገጥ ከቻሉ እንደ ጦር ወንጀል ይቆጠራል\" በማለት ድርጅቱ ማስጠንቀቁ ይታወሳል። በጥቅምት ወር ማብቂያ ላይ የፌደራል መንግሥቱ ሠራዊትና የትግራይ ክልል ኃይሎች ወታደራዊ ግጭት ውስጥ ከገቡ ከሳምንት በኋላ በምዕራብ ትግራይ የተካሄደውን ግጭት ተከትሎ ነበር በማይካድራ ከተማ ውስጥ ሰላማዊ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የሚያመልክቱ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ፎቶግራፎች መታየት የጀመሩት።አምነስቲ ኢንትርናሽናልም የእነዚህን ምስሎች እውነተኝነት በማረጋገጥና የዓይን እማኞችን በማነጋገር በከተማዋ ውስጥ ማንነትን መሰረት ያደረገ አሰቃቂ ጥቃት መፈጸሙን ከሳምንት በፊት ባወጣው መግለጫ ማሳወቁ ይታወሳል። ", "passage_id": "99459df5396441f8808d6046e184df28" }, { "passage": "የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ በባህርዳር፣ ጎንደር፣ ዳንሻ፣ ሁመራና ማይካድራ ከተሞች የመጀመሪያውን ዙር የመስክ ምልከታ ማድረጉን ገልጾ፣ በአከባቢው “በጁንታው” የሕወሓት ቡድን የተፈጸመውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት አብራርቷል፡፡\n\"የጁንታው ቡድን\" በሁመራና በማይካድራ ከተሞች የአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ ትኩረት በማድረግ እጅግ ዘግናኝ ጭፍጨፋ ማድረጉን ቦርዱ በሪፖርቱ አካቷል፡፡\nበተለይ በማይካድራ በአሰቃቂ መንገድ ተገድለው የተገኙ ሰዎች ቁጥር 700 እንደሚደርስ ፣ ነገር ግን በየጫካው እስካሁን ያልተገኙ አስከሬኖች ሊኖሩ እንደሚችሉና በዚህም የሟቾቹ ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ለማ ተሰማ ጠቁመዋል፡፡\n\"ሳምሪ\" የተባለው የወጣቶች ቡድን ይህንን አሰቃቂ ወንጀል ቢፈጽምም ፣ በአንጻሩ የትግራይ ተወላጅ ከሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ገዳዩ ቡድን ሲያሳድዳቸው የነበሩ ሰዎችን በቤታቸው፣ በቤተክርስቲያንና በእርሻ ቦታዎች በመደበቅ የብዙ ሰዎች ህይወት እንዲተርፍ ማድረጋቸውን መርማሪ ቦርዱ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡\nበዳንሻ የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት ቤተሰቦችን በማፈን እንግልት እንደተፈጸመባቸውም ነው ሪፖርቱ የጠቆመው፡፡\n\"ከሃዲው ቡድን\" ለጥፋት ያሰለፋቸውና በመንግስት ቁጥጥር ስር የዋሉ የትግራይ ልዩ ሃይልና የሚሊሻ አባላት\nሰብኣዊ አያያዝ እየተደረገላቸው መሆኑንም መርማሪ ቦርዱ አስረድቷል፡፡\nቦርዱ ጉብኝቱን የጀመረባቸው የባህርዳርና የጎንደር የሲቪል አየር ማረፍያዎች ላይ የደረሰው ጉዳት አነስተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በከተሞቹ በሚገኙ ሆስፒታሎች ለመከላከያ ሰራዊትም ሆነ \"ከሃዲው ቡድን\" ለጥፋት አሰልፏቸው ለቆሰሉ የትግራይ ልዩ ሃይልና ሚሊሻ አባላት ተመሳሳይ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ለማ ተሰማ አስረድተዋል፡፡\nአያይዘውም የጎንደር ከተማ ማህበረሰብና የከተማ መስተዳድሩ ታካሚዎቹን በመንከባከባቸው፤ እንዲሁም ከሀዲው የህወሃት ቡድን ባደረሰባቸው ጥቃት ከትግራይ ክልል በመሰደድ በከተማዋ ለተጠለሉ ተፈናቃዮች ሰብኣዊ ድጋፍ ስለማድረጋቸው አመስግነዋል፡፡\nመሪማሪ ቦርዱ በቀጣይነት በመንግስት ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን ያስቀመጠ ሲሆን፣ ወንጀለኞቹን የማደኑ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና በሱዳን ድንበር አከባቢ ሌላ አደጋ እንዳይፈጠር ጥንቃቄ እንዲደረግ በማለት አሳስቧል፡፡\nበህክምና ላይ ከሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መካከል የባንክ ደብተርና ሌሎች ማስረጃዎች የጠፋባቸው ስለሚገኙ መፍትሄ እንዲሰጥ፣ የተበታተኑ የመከላከያ ሰራዊት ቤተሰቦች እንዲገናኙ ቢመቻች እንዲሁም የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ያለውን በጀት ለተፈጠረው ድንገተኛ አደጋ አሟጦ በመጠቀሙ ድጎማ ቢደረግለት የሚሉ ምክረ ሃሳቦች በመርማሪ ቦርዱ ተሰጥቷል፡፡\nመርማሪ ቦርዱ በቀጣይ ወደ ራያ፣ አላማጣ፣ ሽሬ፣ አክሱም፣ መቀሌና በሌሎች አከባቢዎች ተገኝቶ የምርመራ ስራውን እንደሚያከናውን የቦርዱ ሰብሳቢ ጠቁመዋል፡፡\nዘገባውን ያገኘነው ከሕ/ተ/ም/ቤት የፌስቡክ ገጽ ነው፡፡\n", "passage_id": "91ffd50657b0d548257eafcf0e855ea8" }, { "passage": "በቤንሻንጉል ጉሙዝ  ክልል  በመተከል  ዞን  በአማራ  ተወላጆች ላይ እየተፈጸመ ያለውን  ዘርን መሠረት ያደረገ ጭፍጨፋ፣  የፌዴራል መንግሥት ሥራ በዝቶበት ከሆነና ማስቆም ካልቻለ፣ የአማራ ክልል መንግሥት ጥቃቱን ለማስቆምና ሕግ ለማስከበር ዝግጁ መሆኑን ገልጾ፣ ይሁንታን ለማግኘት ሐሳብ ማቅረቡን አስታወቀ፡፡‹‹በመተከል ዞን እየተፈጸመ ያለውን ጭፍጨፋ የቤንሻንጉል ክልል ባለሥልጣናት ቀን ቀን ስብሰባ ላይ ከእኛ ጋር ሲላቀሱ ይውላሉ፡፡ ማታ ማታ ግን ግድያውን ማስቆም አልቻሉም፤›› በማለት የተናገሩት የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ናቸው፡፡በመተከል ዞን በአማራ ተወላጆች ላይ ዘር እየተመረጠ በየትኛውም ዓለም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ዘግናኝና ጭካኔ በተሞላበት ድርጊት ሰዎች ሲገደሉ፣ የፌዴራል መንግሥት ግዴታና ኃላፊነቱን ካልተወጣ የአማራ ክልል የፀጥታ ኃይል ዝግጁ እንደሆነ ኮሚሽነር አበረ ለሪፖርተር ገልጸዋል።ኮሚሽነሩ  የችግሩን ቀጣይነት አስመልክተው ሲያብራሩ፣ ከአካባቢው አመራሮች ጋር በተደጋጋሚ ውይይት የተደረገ ቢሆንም፣ ‹‹የችግሩ መንስዔዎች ቀን ቀን አብረውን ስብሰባ ላይ ሲላቀሱ ውለው፣ ማታ ግድያውን ማስቆም የተሳናቸው የሕወሓት ርዝራዦች ናቸው፤›› ብለዋል።‹‹አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች የሚገደሉት አማራ ተብለው ስለሆነ ምናልባት የፌዴራል መንግሥት ሥራ በዝቶበት ከሆነ፣ ለእኛ ይስጠን ብሎ ክልሉ ለፌዴራል መንግሥት ሐሳብ አቅርቧል፤›› ሲሉ ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።አንድ ክልል የራሱን የፀጥታ ችግር ማስከበር ካልቻለ የፌዴራል መንግሥት ኃላፊነትና ግዴታ አለበት ያሉት ኮሚሽነሩ፣ ‹‹አቅጣጫ ያስቀምጥልን፣ ሕዝባችን እንታደግ፤›› ሲሉም የፌዴራሉን መንግሥት ጠይቀዋል።‹‹እንደ ክልል ልናደርግ የምንችለው ወደ ፌዴራል መንግሥት አቤት ማለት ነው፡፡ ነገር ግን አሁንም በአማራ ክልል በኩል የሕዝብን ደኅንነት ለማስጠበቅ ዝግጁ ነን፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡የፌዴራል መንግሥት ከፈቀደ ‹‹የአማራ ክልል የአቅም ውስንነት የለበትም›› ያሉት ኮሚሽነር አበረ፣ በሕወሓት ኃይሎች ላይ እንደተደረገው ዘመቻ ከመከላከያ ጋር በመሆን ሥራውን ለማከናወን ፍላጎት እንዳለ ተናግረዋል፡፡ኮሚሽነሩ አክለውም በአገሪቱ ሕገ መንግሥት መሠረት ሁሉም ኢትዮጵያዊ  ማንም  ይሁን ማን፣ በየትኛውም ቦታ እኩል የመኖር መብት አለው ብለዋል። ‹‹ነገር ግን በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ውስጥ ያሉ የወያኔ ተላላኪዎች ሰው ሲገደል ከመከላከል ይልቅ፣ ለምን ተገደለ ብላችሁ ጠየቃችሁን ብለው ያኮርፋሉ፡፡ እንዲህ ዓይነት አካላት የተሰባሰቡበት የአመራር ቡድን በመሆኑ የሰውን ሕይወት ለመታደግ ሲሠሩ አይታዩም፤›› ብለዋል። የአማራና የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልሎች የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በጉዳዩ ላይ እየመከሩ እንደሆነ የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ ‹‹ለችግሩ መፍትሔ ያመጣሉ ብለን እናስባለን፡፡ ነገር ግን እንደ ክልል የፀጥታ ኃይል ትዕዛዝ እየተጠባበቅን እንገኛለን፤›› ብለዋል።", "passage_id": "f2b533b95051db756f9d4476f8907643" }, { "passage": "በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ በርካታ ዜጎች ተገድለዋል የሚል ሪፖርት መውጣቱን ተከትሎ \"ግድያዎቹ መረጋገጥ ከቻሉ እንደ ጦር ወንጀል ይቆጠራል\" በማለት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስጠንቅቋል።ጥቃት የደረሰባቸው እነማን ናቸው?የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኃላፊ ሚሼል ባችሌት በማይካድራ ከተማ ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት ተገድለዋል የሚለው ሪፖርትም እንዲጣራ ጠይቀዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ጭፍጨፋውን የፈፀሙት የህወሓት ታጣቂዎች ናቸው ቢሉም የትግራይ ክልል ባለስልጣናት በበኩላቸው በግድያዎቹ እጃችን የለበትም በማለት ውድቅ አድርገውታል።የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ውንጀላዎቹ \"መሰረት\" የሌላቸው ናቸው ማለታቸውንም አጃንሰ ፍራንስ ፕሬስ እሳቸውን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በበኩላቸው የፌደራል መንግሥት የምዕራብ ትግራይን \"ነፃ ካወጣ\" በኋላ የህወሓት ታጣቂዎች በማይካድራ ከተማ በርካታ ንፁሃን ዜጎችን \"በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለዋል\" ብለዋል።የማይካድራ ከተማ በትግራይ ክልል ደቡብ ምዕራብ ዞን ትገኛለች።የግድያውን ሪፖርት ያወጣው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ግድያውን ማን እንደፈጸመው ለማረጋገጥ አለመቻሉን አመልክቷል። ነገር ግን ያነጋገራቸው የአይን እማኞች ከፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት ጋር የሚዋጉትን የህወሓት ታማኝ ኃይሎች ጥቃቱን እንደፈጸሙ ይከሳሉ።ግድያዎቹ መረጋገጥ ከቻሉም በፌደራል መንግሥትና በትግራይ ክልል መካከል በተነሳው ጦርነት የተገደሉ በርካታ ንፁሃን ዜጎች ያደርጋቸዋል። ከሳምንት በላይ ባስቆጠረው ግጭት በትግራይ ክልል የስልክም ሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት ባለመኖሩ ስለ ግጭቱ መረጃ ለማግኘት አዳጋች አድርጎታል።ሚሼል ባችሌት እንዳሉት በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ሁኔታ ስጋት እንደፈጠረባቸው ጠቅሰው \"ከዚህ በበለጠ ግፎች ከመፈፀማቸው በፊት ለመከላከል ያስችል ዘንድ የውጊያው መቆም ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ ነው ብለዋል።እንደ አምነስቲ ሪፖርት ከሆነ ግድያዎቹ የተፈፀሙት ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም ምሽት ነው።በማይካድራ ከተማ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በስለት ተወግተው ወይም ተቀጥቅጠው እንደተገደሉ አምነስቲ አረጋግጫለሁ ብሏል። በከተማዋ \"በየቦታው ወድቀው የሚታዩና በአልጋ ላይ የሚታዩ አስከሬኖችን አሰቃቂ ፎቶግራፎችና ቪዲዮዎችን የተረጋገጡ\" ናቸው ብሏል።ጥቃት የደረሰባቸው ግለሰቦች የቀን ሰራተኞች እንደሚመስሉ የተጠቀሰ ሲሆን በግጭቱም ምንም አይነት ተሳትፎ የላቸውም ብሏል። ከየት እንደመጡም ማረጋገጥ እንዳልተቻለም ድርጅቱ አክሎ ገልጿል።የአይን እማኞችን ዋቢ አድርጌያለሁ ያለው አምነስቲ \"ጥቃት የደረሰባቸው ግለሰቦች በስለታማ ነገሮች ለምሳሌም ያህል በቢላና በቆንጨራ ነው\" ብለዋል።አንዳንድ የአይን እማኞች ከፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት ጋር የሚዋጉትን የህወሓት ታማኝ ኃይሎች ሉግዲ በምትባል ቦታ መሸነፋቸውን ተከትሎ ጥቃቱን እንደፈጸሙ ይከሳሉ። የትግራይ ክልል ይህንን \"መሰረት\" የለውም በሚል አልተቀበለውም።ከዚህም በተጨማሪ በመቀለና በአዲግራት በደረሰ የአየር ጥቃት ንፁሃን ዜጎች መገደላቸውን ደብረፅዮን (ዶ/ር) ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ተናግረዋል።\"በርካቶች በየአቅጣጫው በመሮጥ ሸሽተዋል። የዚህ ግጭት ዋነኛ መዘዝ መፈናቀል ነው። እውነት ነው የሞቱም ሆነ የተጎዱ ሰዎች አሉ። ነገር ግን እስካሁን ቁጥሩን አናውቅም። ይህን ለመቆጣጠር በጣም ትልቅ ነው\" ማለታቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ አስነብቧል።ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሻከረ የመጣው የፌደራልና የትግራይ ክልል መንግሥት ግንኙነት የማይታረቅ ደረጃ ደርሶ ከሳምንት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የትግራይ ልዩ ኃይል በክልሉ የሚገኘውን የመከላከያ ሰሜን ዕዝ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልፀው ጦርነት መከፈቱን አስታውቀዋል።ጠቅላይ ሚንስትሩ በአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው የመከላከያ ሠራዊት በኮማንድ ፖስት እየተመራ \"አገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል\" ብለዋል።የትግራይ ክልል በበኩሉ በክልሉ የሚገኙት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰሜን ዕዝ ሰራዊት አባላትና አዛዦች ከትግራይ ክልል መንግሥት ጎን ለመሰለፍ ወስነዋል ማለቱ ይታወሳል።ከዚህም በተጨማሪ የፌደራል መንግሥት የአየር ጥቃትም እያደረሰ ነው ተብሏል።በዚህም ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ወደ ጎረቤት አገር ሱዳን የተሰደዱ ሲሆን የሱዳን መንግሥትም በስደተኞች መጠለያ ካምፕ ውስጥ አስገባቸዋለሁ ብሏል።", "passage_id": "e04374baea13aabd1d655deb69bba767" } ]
95cb9e8664c2e8508162c96aace57e72
e3a7c8765c1837ce08ffd1f1a47bb24c
የቦስተን ማራቶን አሸናፊዎች ከዓለም ቻምፒዮኖች ጋር ይፋለማሉ
ከዓለም ምርጥ የማራቶን ውድድሮች መካከል አንዱ የሆነው የቦስተን ማራቶን ከዚህ ቀደም ማሸነፍ የቻሉና የዓለም ቻምፒዮን የሆኑ አትሌቶች ዘንድሮ የሚፋለሙበት በመሆኑ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል። የዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ የሰጠው ይህ ውድድር በተለይ በሴቶች ምድብ ባለ ክብረወሰኗን ኢትዮጵያዊት አትሌት ወርቅነሽ ደገፋን ጨምሮ ከዓለም ዙሪያ የተሰባሰቡ አምስት ከ2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ እንዲሁም አስራ ሁለት 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ በታች ማራቶንን ማጠናቀቅ የቻሉ አትሌቶች ተሳታፊ መሆናቸው ውድድሩን ተጠባቂ አድርጎታል። የአሸናፊነት ቅድመ ግምቱ ለቦታው ባለ ክብረወሰን ለሆነችው አትሌት ወርቅሽ የሚሰጥ ቢሆንም፤ ከባድ ፉክክር የሚገጥማት መሆኑ ውድድሩን ይበልጥ አጓጊ አድርጎታል። እአአ በ2018 የውድድሩ አሸናፊ የነበረችው አሜሪካዊቷ ዴስሬ ሊንደን፣ የሁለት ጊዜ በየዓለም ቻምፒዮናዋ ኬንያዊት ኤድና ኪፕላጋት፣ እአአ በ2015 የቦታው ባለ ድል ካሮላይን ሮቲች እንዲሁም እአአ በ2014 የቦታውን ክብረ ወሰን የሰበረችው ኢትዮጵያዊቷ ብዙነሽ ዳባ የቦስተን ከተማ በምታስተናግደው ታላቁ የጎዳና ላይ ሩጫዋ ድምቀት የሚሆኑና ከ2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ በታች መሮጥ የቻሉ አትሌቶች መሆናቸውን አዘጋጆቹ አረጋግጠዋል። እአአ በ2015 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ነሃስ ሜዳሊያ ባለቤቷ ማሬ ዲባባ እንዲሁም በዚያው ቻምፒዮና የ10 ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ያገኘችው ገለቴ ቡርቃ፣ መስከረም አሰፋ፣ የብርጓል መለሰ፣ በሱ ሳዶ እንዲሁም ሃፍታምነሽ ተስፋይ ደግሞ ሌላኛዎቹ በውድድሩ ጠንካራ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ የሚጠበቁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ናቸው። የ2017ቱ የዓለም ቻምፒዮን ባህሬናዊቷ ሮዝ ቺሊሞ፤ ያለፈው ዓመት የቶሮንቶ ማራቶን አሸናፊዋ ማግዳላይኔ ማሳይ፣ በሮም ማራቶን የሶስት ጊዜ ባለድል ራህማ ቱሳ፣ በ2018 ቦስተን ማራቶንን በሶስተኝነት ያጠናቀቀችው ክሪስታ ዱቼኔ እንዲሁም የሁለት ጊዜ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮናዋ ሜሪ ንጉጊም በዚህ ማራቶን ላይ ተሳታፊ የሚሆኑና ለአሸናፊነቱ ቀላል ግምት የማይሰጣቸው አትሌቶች ናቸው። በወንዶች በኩልም ብርቱ ፉክክር እንደሚኖር ማሳያ የሆኑ አትሌቶች እንደሚካፈሉ የታወቀ ሲሆን፤ ከእነዚህ መካከል አስር የሚሆኑት ማራቶንን 2 ሰዓት ከ07 እና ከዚያ በታች የሆነ ሰዓት ማጠናቀቅ የቻሉ አትሌቶች ናቸው። ያለፈው ዓመት የቦስተንና የቺካጎ ማራቶን አሸናፊው ኬንያዊ አትሌት ላውረንስ ቼሮኖ ክብሩን እንደያዘ ለመቆየት፤ ከዚህ ቀደም የነበሩ የቦስተን ማራቶን አሸናፊ አትሌቶችን መጋፈጥ የግድ ይለዋል። የሁለት ጊዜ የቦስተን ማራቶን አሸናፊውና የዶሃው የዓለም ቻምፒዮና ባለድሉ ሌሊሳ ዴሲሳ ዘንድሮም ሌላ ድል ለማስመዝገብ በቦስተን የሚገኝ መሆኑን አስታውቋል። እአአ የ2017 አሸናፊው ጃፓናዊ ዩኪ ካዋቺ እና የ2018ቱ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ ጂኦፈሪ ኪሩይም በቦታው ድላቸውን ለመድገም ተዘጋጅተዋል። ኡጋንዳዊው የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮን ስቴፈን ኪፕሮቲች፣ አልበርት ኮሪር፣ ኤርትራዊው አብራር ኦስማን፣ ኢትዮጵያውያኑ ደጀኔ ደበላ፣ ፍቅሬ በቀለ፣ ጀማል ይመር እንዲሁም ከሌሎች አገራት የተውጣጡ በርካታ አትሌቶችም በአሜሪካው ግዙፍ የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳታፊ መሆናቸውን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ቅዳሜ ጥር 23/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=26509
[ { "passage": "በ 120ኛው የቦሰተን ማራቶን በሴቶቹ ተከታትለው በመግባት ያሸነፉት፥ አፀደ ባይሣና ትርፊ ነገሪ ናቸው። የወንዶቹን ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ሥፍራ የወሰዱትና ታሪክ የሠሩት የኢትዮጵያ ሯጮች ደግሞ፥ ለሚ ብርሃኑ፥ ያለፉት ሁለት ዓመታት ሻምቲዮኑ ሌሊሣ ዴሢሣና ፀጋዬ ናቸው። አሸናፊዎች አንደኛ የወጣው፥ ዋንጫና $150.000 ሺህ ያሜሪካ ዶላር ሽልማት ወስዷል። ሁለተኛና ሦስተኛ የወጡት ደግሞ ሜዳልያ፥ የ $75 እና የ $40 ሺህ ያሜሪካ ዶላር ቼክ ተቀብለዋል። በዛሬው የቦስተን ማራቶን ውድድር ላይ፥ ከ 50ዎቹም የዩናይትድ ስቴትስ ክፍለ ግዛቶችና ከ 81 ሀገሮች የመጡ አትሌቶች፥ በጠቅላላው 30 ሺህ ሯጮች ተሳትፈዋል። የፀጥታ ጥበቃው ከመቼውም በበለጠ በሚያይና በማይታይ መልኩ ተጠናክሮ እንደነበር ተዘግቧል። ", "passage_id": "da93c2d3952c34c9c6a548dc86a78abd" }, { "passage": "የዓለማችን ታላላቅ ከተሞች በየዓመቱ ከሚያ ስተናግዷቸው በርካታ የማራቶን ውድድሮች በሚያፎካክራቸው አትሌቶች ደረጃና ጥራት ቀዳሚ ሆኖ የሚገኘው የለንደን ማራቶን ነው። ይህ ውድድር የፊታችን እሁድ ሲካሄድ እንደተለመደው በርቀቱ ስመ ጥር የሆኑ በርካታ አትሌቶችን በሁለቱም ፆታ ለማፎካከር ተዘጋጅቷል። ባለፉት ሦስት ዓመታት በኬንያዊው የርቀቱ ፈርጥና የዓለም ክብረወሰን ባለቤት ኢሉድ ኪፕቾጌ የበላይነት ተይዞ የቆየው የለንደን ማራቶን ዘንድሮ በአገሩና በደጋፊው ፊት በሚሮጠው ሞሐመድ ፋራህ ይደምቃል ተብሎ ይጠበቃል። የዘንድሮው ውድድር በሦስት ጊዜ ባለ ድሉ ኪፕቾጌና በፋራህ መካከል የሚደረገው ፉክክር ከወዲሁ ትኩረት ቢያገኝም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርቀቱ አስደናቂ ብቃት እያሳዩ በሚገኙት ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ሹራ ቂጣታ፣ ሞስነት ገረመውና ልዑል ገብረሥላሴ የበለጠ እንደሚደምቅ ይጠበቃል። በሁለት ኦሊምፒኮችና በሦስት የዓለም ቻምፒዮናዎች የአምስትና አስር ሺ ሜትር ንጉሥ ሆኖ መዝለቅ የቻለው ሞ ፋራህ ካለፈው ዓመት ወዲህ ፊቱን ወደ ማራቶን መመለሱ ይታወቃል። ባለፈው የለንደን ማራቶን ሦስተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ፋራህ ጥቅምት ወር ላይ በቺካጎ ማራቶን በ2:05:11 የአውሮፓን ክብረወሰን አስመዝግቦ የመጀመሪያ ድሉን ካጣጣመ ወዲህ የዓለማችን የወቅቱ ኮከብ የማራቶን አትሌቶችን ጎራ ተቀላቅሏል። ድንቅ የማራቶን አትሌት መሆኑን ለማወጅም የእንግሊዝ መገናኛ ብዙኃን የእሁዱን የለንደን ማራቶን ድል አሰፍስፈው እየጠበቁ ይገኛሉ። ጥያቄው ግን ሌላው ይቅርና ፋራህ ኪፕቾጌን ማቆም እንዴት ይቻለዋል ነው? አንዳንድ የአገሬው መገናኛ ብዙኃን ኪፕቾጌ ምንም ያህል የርቀቱ ኮከብና ባለ ክብረወሰን ቢሆን ከእድሜው መግፋት ጋር ተያይዞ አንድ ቀን እጅ እንደሚሰጥ እርግጠኛ ሆነዋል። ያም ቀን የፊታችን እሁድ ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን እያስቀመጡ ነው። ያም ሆኖ ኪፕቾጌ አሁን ያለው አቋም ካለፈው ዓመት አኳያ የተሻለ እንጂ የባሰ እንደማይሆን ከልምምዶቹ መረዳት ይቻላል። ኪፕቾጌ ባለፈው ዓመት ወደ ተመሳሳይ ውድድር ከመምጣቱ በፊት በተለያዩ ውድድሮች ማራቶንን ከ2፡00 በታች ለማጠናቀቅ ብዙ ጥረት አድርጎ ነበር። ይህም ከአቅሙ በላይ ጉልበቱን እንዲያሟጥጥ አድርጎታል በሚል የለንደን ማራቶንን እንደማያሸንፍ ተጠርጥሮ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ድንቅ ኬንያዊ ለሦስተኛ ጊዜ ለንደን ላይ ነግሷል። ከዚያም ባለፈ ባለፈው የበርሊን ማራቶን 2:01:39 የሆነውን የዓለም ክብረወሰን በአስደናቂ ብቃት የግሉ ማድረግ ችሏል። ኪፕቾጌ በርሊን ላይ ያስመዘገበው ክብረሰወን የብቃቱ ጥግ ነው። ይህን ብቃቱን ዘንድሮ ላይደግመው ቢችል እንኳን ባለፉት ሦስት የለንደን ማራቶኖች ሲያሸንፍ ያስመዘገባቸው ሰዓቶች በአማካኝ ሲሰሉ 2:04:01 ነው። ታዲያ ፋራህም ይሁን ሌሎቹ ጠንካራ ተፎካካሪዎች ይህን እንዴት መመከት ይቻላቸዋል የሚሉ የስፖርቱ ቤተሰቦች በርካታ ናቸው። ኪፕቾጌ የዓለም ክብረወሰን የሆነውን ሰዓት ማስመዝገብ የቻለው በሂደት እየበሰለ መጥቶ በአስራ አንደኛው የማራቶን ውድድሩ ነው። እድሜው ሰላሳ አራት ሲሆን ሞ ፋራህን በሁለት ዓመት ብቻ ይበልጠዋል። ፋራህ እንደ ቀደምቶቹ ኮከብ አትሌቶች ወደ ማራቶን የመጣው በርካታ ዓመታትን በመም ውድድሮች አልፎ መሆኑ በማራቶን ጥሩ አትሌት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ባለፈው ዓመት በመጀመሪያ የማራቶን ውድድሩም ሦስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ የነበረው በራስ መተማመንና በልምድ የሚበልጡትን የስነ ልቦና ጫና መቋቋም መቻሉ ዘንድሮ የተሻለ ነገር እንዲያሳይ ይረዳዋል የሚል መደምደሚያ ላይ አድርሷል። ሁለቱ ታላላቅ አትሌቶች ቀድመው ከገነቡት ስም አኳያ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን በፉክክሩ ግንባር ቀደም ሆነው ይጠቀሱ እንጂ ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ያልተገመተ ነገር ሊፈጥሩ እንደሚችሉ መጠበቅ ያስፈልጋል። በተለይም ባለፈው ዓመት በዚሁ ውድድር ኪፕቾጌን ተከትሎ ሁለተኛ በመሆን ያጠናቀቀው ሹራ ቂጣታ ፋራህን በ1፡ 32 ሰከንድ ልዩነት ቀድሞ መግባቱ ሊሰመርበት ይገባል። በሌላ በኩል ባለፈው የዱባይ ማራቶን የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል ያሸነፋው ሞስነት ገረመው ፋራህ በቺካጎ ማራቶን ሲያሸንፍ በአስራ ሦስት ሰከንዶች ዘግይቶ ሁለተኛ ማጠናቀቁ በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ሌላኛው ትኩረት የሚሰጠው ኢትዮጵያዊ ልዑል ገብረሥላሴ ባለፈው ዓመት ማራቶንን ከ2፡05 በታች ማጠናቀቅ ከቻሉ ሦስት አትሌቶች አንዱ እንደመሆኑ ቀላል ተፎካካሪ አይሆንም። ይህ አትሌት በዱባይ ማራቶን 2፡ 04፡02 ያስመዘገበ ሲሆን ቫሌንሲያ ላይ 2፡04፡ 31 በሆነ ሰዓት የቦታውን ክብረወሰን ማሻሻል ችሏል። ስለዚህ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ከፋራህ ይልቅ ለኪፕቾጌ አስፈሪ ሊሆኑ የሚችሉት ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ናቸው። እንደ ዘንድሮው የለንደን ማራቶን የትኛውም የማራቶን ውድድር በሴቶች ድንቅ የሆነ ፉክክር እንደማይታይ ከወዲሁ እየተነገረ ነው። በሴቶች መካከል ተፎካካሪ የሚሆኑት አትሌቶች ባለፈው ጥር ይፋ ሲደረጉ ከ2018 የወርልድ ማራቶን ሜጀርስ (WMM) ስድስት አሸናፊዎች አምስቱ መካተታቸው ጉድ ተብሎለት ነበር። ከነዚህ በተጨማሪ የ2018 የዱባይ ማራቶን ቻምፒዮንና በታሪክ በርቀቱ ፈጣን ከሆኑት አምስት አትሌቶች አራቱ መካተታቸው የዘንድሮውን የለንደን ማራቶን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ተጠባቂ አድርጎታል። ከዚያን ጊዜ ወዲህ ግን የተቀየሩ ነገሮች መኖራቸው አልቀረም። የረጅም ርቀት ንግስቷ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ሁለተኛ ልጇን እንደ ፀነሰች መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ የዘንድሮው የለንደን ማራቶን የሴቶች ፉክክር ላይ ቀድሞ የነበረው አሰላለፍ እንደሚቀየር ይጠበቃል። ቀደም ሲል የዓለማችን ሁለተኛ፣ ሦስተኛ፣ አራተኛና አምስተኛ ፈጣን ሰዓት ባለቤት የሆኑ አትሌቶች እንደሚፎካከሩበት የተነገረው ውድድር አሁን ሁለተኛ፣ ስድስተኛ፣ ሰባተኛና ዘጠነኛ ፈጣን ሰዓት ያላቸው አትሌቶች የሚፎካከሩበት ሆኗል። የሦስት ጊዜ የለንደን ማራቶንና የአራት ጊዜ የኒውዮርክ ማራቶን አሸናፊዋ ኬንያዊት ማሪ ኪታኒ የዘመኗ ምርጥ አትሌት ነች። ይህም በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ቀዳሚ የትኩረት ማረፊያ አድርጓታል። የኦሊምፒክ 5ሺ ሜትር ቻምፒዮኗ ቪቪያን ቼሪዮት ያለፈው ለንደን ማራቶን አሸናፊና የኒውዮርክ ማራቶንን ሁለተኛ ሆና ያጠናቀቀች አትሌት መሆኗ በሁለተኛነት ትኩረት አሰጥቷታል። 2:18:11 በሆነ ሰዓት የበርሊን ማራቶንን ክብረወሰን የጨበጠችው ግላዲ ቺሮኖ ትልቅ ትኩረት ያገኘች ሌላኛዋ ኬንያዊት ነች። እነዚህ ግዙፍ ስም ያላቸው ኬንያውያን ከእነሱ እኩል አቅም ያላቸውን የዘወትር ተፎካካሪ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚፎካከሩበት ውድድር አጓጊ ባይሆን ይገርማል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማራቶን ጎልቶ የሚጠራ የኢትዮጵያውያን ስም መካከል ሮዛ ደረጄ አንዷ ናት። 2:19:17 በሆነ ሰዓት ባለፈው ዓመት የዱባይ ማራቶን ክብረወሰንን ሰብራለች። ባለፈው የካቲት ደግሞ በባርሴሎና ግማሽ ማራቶን 66፡01 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችላለች። ሮዛ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ለኬንያውያን ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል። ባለፈው ቶኪዮ ማራቶን 2:19:51በሆነ ሰዓት ስታሸንፍ የቦታውን ክብረወሰን በአራት ሰከንዶች ከማሻሻል የቀረችው ብርሃኔ ዲባባ በእሁዱ ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ እንደምትሆን ትጠበቃለች።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 17/2011 ", "passage_id": "f9e47a6c3e9aba6b3a6876efad7b1929" }, { "passage": " ኢትዮጵያ በአትሌቲክስ ስፖርት በተለይ ከምትታወቅባቸውና ውጤታማም ከሆነችባቸው ርቀቶች መካከል ይጠቀሳል፤ 5ሺ ሜትር። ከሁለት ዓመታት በፊት በለንደን በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ኢትዮጵያ በአትሌት ሙክታር እንድሪስ አማካኝነት የርቀቱ ቻምፒዮን መሆኗ ይታወሳል። በቅርቡ በተጠናቀቀው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይም በተመሳሳይ የዓለም ፈጣኑ ሰዓት የተመዘገበው በኢትዮጵያዊ አትሌት መሆኑ ይታወቃል። ይህም ከተጀመረ ዛሬ አራተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የዶሃ ዓለም ቻምፒዮና ላይ የርቀቱን ቀዳሚ የአሸናፊነት ግምት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች እንዲያገኙ አድርጓል። በዚህ ውድድር ተጋባዥ ከሆነው ቻምፒዮኑ ሙክታር ባሻገር፤ ጥላሁን ኃይሌ፣ ሰለሞን ባረጋ፣ እንዲሁም አባዲ ሃዲስ አገራቸውን የሚወክሉ አትሌቶች ናቸው። ይሁን እንጂ አባዲ ሃዲስ ማጣሪያውን ማለፍ አልቻለም። ቀሪዎቹ አትሌቶች በግላቸው ያስመዘገቧቸው ሰዓቶች በርቀቱ ከሚሳተፉት አትሌቶች ሁሉ ፈጣን መሆኑ፤ የርቀቱ ክብር ዘንድሮም ከምሥራቅ አፍሪካውያኑ እጅ እንደማይወጣ ያመላከተ ሆኗል። በሦስት ቻምፒዮናዎች ላይ በተከታታይ መንገስ የቻለው እንግሊዛዊው አትሌት ሞ ፋራህ ዘመን ከማብቃቱ ጋር በተያያዘም ሜዳሊያው የኢትዮጵያውያን ስለመሆኑ ግምታቸውን የሚያስቀምጡም በርካታዎች ናቸው። ኢትዮጵያ በቻምፒዮናው እስካሁን ድረስ ወርቅ አለማስመዝገቧን ተከትሎም እነዚህ ወጣት አትሌቶች የመጀመሪያው የወርቅ ሜዳሊያ ተስፋ ሆነዋል። ሞ ፋራህን በመጨረሻው\nየመም ውድድሩ የረታው\nየዓለም ቻምፒዮኑ ሙክታር\nእድሪስ በዚህ ቻምፒዮና\nላይ ተጋባዥ ቢሆንም\nበጉዳት ምክንያት በዛሬው\nውድድር ተሳታፊ ላይሆን\nእንደሚችል ተገምቶ ነበር።\nይሁን እንጂ ሙክታር\nማጣሪያውን አልፎ ዛሬ\nበፍፃሜ ተፋላሚ እንደሚሆን\nአረጋግጧል። የሁለት ጀግና አትሌቶችን ስም አጣምሮ የያዘው ወጣቱ አትሌት ጥላሁን ኃይሌ በቀለ ለአሸናፊነት ከሚጠበቁት መካከል አንዱ ሲሆን፣ በሮም ዳይመንድ ሊግ ያስመዘገበው\n12:52.98 የሆነ ሰዓት በዛሬው ውድድር ላይ የሚካፈሉት አትሌቶች ሁሉ ፈጣኑ ነው። በለንደኑ ቻምፒዮና በርቀቱ\nአምስተኛ ደረጃን በመያዝ\nያጠናቀቀው ሌላኛው ወጣት\nአትሌት ሰለሞን ባረጋም\nበዚህ ውድድር የአሸናፊነት\nቅድመ ግምት ያገኘ አትሌት ነው። አትሌቱ እአአ በ2018 ያስመዘገበው ፈጣን ሰዓት 12:43.02 ከርቀቱ ተሳታፊዎች ሁለተኛው ምርጥ ሰዓት ነው። ሰለሞን የዓለም ቻምፒዮና ተሳትፎው ይህ ሁለተኛው መሆኑ የተሻለ ልምድ እንደሚያስገኝለት የሚታመን ሲሆን፤ ለፈጣኑ ሰዓት ያለው ቅርበትም የወርቅ ሜዳሊያውን ለማጥለቅ የሚሮጥ ያሰኘዋል። ባህሬናዊው ብርሃኑ ባለው\n12:56.26 ሰዓት በማስመዝገብ ኢትዮጵያውያኑን አትሌቶች የሚከተል ከመሆኑ ባሻገር ለኢትዮጵያውያኑ ፈተና እንደሚሆንባቸውም ይጠበቃል። ኮማንደር ቶሌራ ዲንቃ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር አሰልጣኝ፤ ርቀቱ በዓለም ላይ ፈጣን ሰዓት ባላቸው አትሌቶች የተዋቀረ መሆኑን ይጠቁማሉ። አዳዲስና ጥሩ ሰዓት ያላቸው ወጣት አትሌቶች ተሳታፊ የሚሆኑበትም ነው። በተጨማሪም ሁሉም አትሌቶቹ በዓመቱ ዳይመንድ ሊግ ላይ ርቀቱን በደንብ የሸፈኑ አትሌቶች መሆናቸው ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚረዳቸው በዝግጅታቸው ወቅት ለአዲስ ዘመን ገልጸዋል። በዓለም ቻምፒዮና በ5ሺ ሜትር የኢትዮጵያ ታሪክ እ.አ.አ 1991 ቶኪዮ ላይ ይጀምራል፤ በወቅቱ ፊጣ ባይሳ ኬንያዊውን አትሌት ተከትሎ በመግባት የብር ሜዳሊያ ነበር ያገኘው። ከሁለት ዓመታት በኋላም በስቱትጋርት ኃይሌ ገብረስላሴ እና ፊጣ ባይሳ ተከታትለው በመግባት የብርና የነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚዎች ሆነዋል። እ.አ.አ 2001 ኤድመንተን ላይ በተካሄደው ቻምፒዮና ሚሊዮን ወልዴ ሦስተኛውን የብር ሜዳሊያ እስካስመዘገበበት ጊዜ ድረስም ኢትዮጵያ በሦስት መድረኮች ከሜዳሊያ ሰንጠረዥ መግባት አልቻለችም ነበር። እ.አ.አ 2003 ቀነኒሳ በቀለ የነሐስ፣ ሄልሲንኪ በስለሺ ስህን የብር፣ በርሊን በቀነኒሳ የወርቅ፣ ዴጉ በደጀን ገብረመስቀል የነሐስ፣ ሞስኮ እና ቤጂንግ ሐጎስ ገብረሕይወት ብርና ነሐስ እንዲሁም ለንደን ላይ ሙክታር እድሪስ የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቁ አትሌቶች ናቸው። በርቀቱ ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ኬንያ በርካታ ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ቀዳሚ ስትሆን፤ 14ሜዳሊያዎችን ወደ ካዝናዋ አስገብታለች። አምስት ሜዳሊያዎች ያሏት እንግሊዝ ደግሞ በወርቅ ሜዳሊያ ብዛት ሁለተኛ ስትሆን፤ በተከታይነት ኢትዮጵያ 2የወርቅ፣ 5የብር እና 4የነሐስ በጥቅሉ 11ሜዳሊያዎችን በወንድ አትሌቶች በማግኘት ሦስተኛ ስፍራ ላይ ተቀምጣለች። በዓለም ቻምፒዮናው የርቀቱ ክብረወሰን እ.አ.አ በ2003 የተመዘገበው\n12:52.79 ሲሆን፤ ኬንያዊው አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ ደግሞ የሰዓቱ ባለቤት ነው። ሌላው ዛሬ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚካፈሉበት ርቀት የ3ሺ ሜትር መሰናክል ሴቶች ምድብ ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር እ.አ.አ 2013ቱ የሞስኮ ቻምፒዮና ነበር የነሐስ ሜዳሊያ በአትሌት ሶፊያ አሰፋ ያስመዘገበችው። ሶፊያ በዚህ ርቀት በ2012ቱ የለንደን ኦሊምፒክም ሦስተኛ የወጣች ቢሆንም፤ ቀድማት የገባችው አትሌት የአበረታች ቅመም ተጠቃሚነቷ በመረጋገጡ የብር ሜዳሊያውን ሶፊያ እንድትወስድ ተደርጓል። በዘንድሮው ቻምፒዮና ላይ አትሌት መቅደስ አበበ፣ ሎሚ ተፈራ፣ ዘርፌ ወንድምአገኝ እና አገሬ በላቸው ኢትዮጵያን ይወክላሉ። የ3ሺ ሜትር መሰናክል አሰልጣኝ ተሾመ ከበደ፤ አትሌቶቹ በራባት የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ ተሳታፊ በመሆናቸው ረዘም ላለ ጊዜ በሳምንት ስድስት ቀን በቀን ደግሞ ለሁለት ጊዜ በዝግጅት ላይ መቆየታቸውን ተናግሯል። በሄንግሎ በተካሄደው የሰዓት ማሟያ ውድድር ላይ የተመዘገበው ጥሩ ሰዓት መሆኑን የጠቆሙት አሰልጣኙ፤ በርቀቱ ያለውን ታሪክ ለመቀየር ቡድኑ ወደ ዶሃ ያመራ መሆኑንም አስረድተዋል። በዚህ ርቀት ኬንያውያን አትሌቶች ስኬታማ ሲሆኑ ባትሬክ ቼፕኮች ደግሞ በለንደን ቻምፒዮን መሆኗ አይዘነጋም። አትሌቷ ከ2018 ጀምሮ በተሳተፈችባቸው 17 ውድድሮች 15ቱን ያሸነፈች ጠንካራ አትሌት ስትሆን፤ በተያዘው ዓመት ያስመዘገበችው 8:55.58 የሆነ ሰዓት ደግሞ ፈጣኑ ነው። 9:03.71ሰዓት ያላት ኖራህ ጀሩቶ በ3ሺ ሜትር መሰናክል የአሸናፊነት ግምት እንዲሁም ፈጣን ሰዓት ያላቸው ኬንያውያን አትሌቶች ሁለተኛዋ ናት። እ.አ.አ የ2015 ቻመፒዮኗ ሃይቪን ኪያንግ 9:03.83 በሆነ ሰዓት ሦስተኛዋ ፈጣን አትሌት ናት። ለንደን ላይ ቻምፒዮን የነበረችው አሜሪካዊቷ ኤማ ኮቡርን አራተኛው ፈጣን ሰዓት ያላት ስትሆን፤ ከኬንያውያኑ አትሌቶች ጋር ብርቱ ፉክክር እንደምታደርግም ይጠበቃል።አዲስ ዘመን  መስከረም 19/2012 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "8783d01e57a66da3bce79909914663e3" }, { "passage": " በፊንላንድ ሄልሲንኪ ከተማ እኤአ በ1983 የተጀመረው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የዓለማችን ትልቁ የአትሌቲክስ መድረክ በመሆን ያለፉትን አርባ ዓመታት አሳልፏል። እኤአ በ1987ና 1991 በአራት ዓመት ልዩነት የጣሊያኗ መዲና ሮምና የጃፓኗ ቶኪዮ ይህን ታላቅ ውድድር ያዘጋጁ አገሮች ናቸው። ከቶኪዮ ወዲህ ግን ውድድሩ በሁለት ዓመት ልዩነት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። የጀርመኗ ስቱትጋርት፤ የስዊድኗ ጉተንበርግ፤ የግሪኳ አቴንስ፤ የስፔኗ ሴቪሊ፤ የካናዳዋ ኤድመንተን፤ የፈረንሳይ መዲና ፓሪስ፤ የፊንላንዷ ሄልሲንኪ (ለሁለተኛ ጊዜ) የጃፓኗ ኦሳካ፤ የጀርመኗ በርሊን፤ የደቡብ ኮሪያዋ ዴጉ፤ የሩሲያዋ ሞስኮና የቻይናዋ ቤጂንግና የእንግሊዟ ለንደን ቻምፒዮናውን በሁለት ዓመት ልዩነት በቅደም ተከተል መድረኩን አዘጋጅተውታል። የዘንድሮ ተረኛዋ የካታሯ ዶሃ ስትሆን የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን ትኩረት ቢነፍጓትም ከአምስት ወራት በኋላ ለሚጠብቃት ታላቅ የስፖርት ድግስ ሽርጉድ ማለት ጀመራለች። የአሜሪካዋ ዩጂንም ቀጣዮን ቻምፒዮና ለማዘጋጀት ወረፋ ይዛለች። ኢትዮጵያም ቻምፒዮናው ከተጀመረ አንስቶ በመሳተፍ ላይ ትገኛለች። የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና አሁን ያለውን መልክ ይዞ መካሄድ ከመጀመሩ በፊት እኤአ በ1913 የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር ኦሊምፒክ እንደ ዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ያገለግላል ብሎ አምኖበት ነበር። ይህም ለሃምሳ ዓመታት ያህል አገልግሎ 1960ዎቹ ውስጥ በርካቶቹ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር አባል አገሮች «የራሳችን የሆነ ውድድር ይኑረን» ብለው ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት እኤአ በ1976 ፑርቶሪኮ ላይ በተደረገ ዓመታዊ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር ስብሰባ ላይ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከኦሊምፒክ ተለይቶ ራሱን የቻለ ውድድር እንዲያካሂድ ተወሰነ። በእዚህን ወቅት የመጀመሪያውን ውድድር ለማስተናገድ የምዕራብ ጀርመኗ ስቱትጋርትና የፊንላንዷ ሄልሲንኪ ጥያቄ አቀረቡ። እኤአ በ1952 ኦሊምፒክን ያስተናገደችው ሄልሲንኪ እድሉን አገኘች። የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በውድድር አይነትና በተሳታፊዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በርካታ ለውጦችን አስተናግዷል። እኤአ በ1983 ከመቶ 54 አገራት የተውጣጡ1 ሺ 300 አትሌቶች ተሳታፊ ነበሩ። ይህ ቁጥር እኤአ 2003 ፓሪስ ላይ ተካሂዶ በነበብቻ ሳይሆን በተለያዩ የውድድር አይነቶችም በርካታ ለውጦች ታይተዋል። በተለይም ወንዶች በሚወዳደሩባቸው የውድድር አይነቶች ሴቶችም ተካፋይ እንዲሆኑ መደረጉ የቻምፒዮናው ትልቅ ለውጥ ነው። አሁን ላይ በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ወንዶች የሚወዳደሩበት ለሴቶች ያልተፈቀደ የሃምሳ ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ብቻ ነው። እኤአ በ1987 የሴቶች አስር ሺ ሜትር ሩጫና አስር ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር የዓለም ቻምፒዮናን የተቀላቀለ አዲስ የውድድር አይነት ነው። ከስድስት ዓመት በኋላም የሴቶች ስሉስ ዝላይ የውድድሩ አካል ሆኗል። እኤአ በ1995 የሴቶች አምስት ሺ ሜትር ሩጫ የሦስት ሺ ሜትርን ወክሎ የውድድር አካል ሆነ። እኤአ በ1999 ደግሞ የሴቶች ምርኩዝ ዝላይና መዶሻ ውርወራ የውድድር አካል ከመሆናቸው በተጨማሪ የሴቶች አስር ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር በሃያ ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር ተተካ። እኤአ በ2005 የሴቶች ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል ውድድር ተጨመረ። የለንደኑን ቻምፒዮኗ ሳይጨምር ባለፉት 15 ረው ቻምፒዮና ከሁለት መቶ ሦስት አገሮች የተውጣጡ 1 ሺ 907 አትሌቶች አሻቅቧል። በዓለም ቻምፒዮና የተሳታፊዎች ቁጥር የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናዎች 98 አገራት የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ 2036 ሜዳሊያዎች (670 የወርቅኸ 685 የብርና 681 የነሐስ) ለአሸናፊዎች ተበርክተዋል፡፡ ከ16ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በፊት የምንጊዜም የሜዳሊያ ስብስብ ደረጃን በድምሩ 323 ሜዳሊያዎች (143 የወርቅ፤ 96 የብርና 84 የነሐስ) በመሰብሰብ አሜሪካ አንደኛነቷን አስጠብቃለች፡፡ ሩሲያ 172 ሜዳሊያዎች (55 የወርቅ ፤ 60 የብርና 57 የነሐስ)፤ ኬንያ 128 ሜዳሊያዎች (50 የወርቅ፤ 43 የብርና 35 የነሐስ) ፤ ጀርመን 108 ሜዳሊያዎች (33 የወርቅ፤ 35 የብርና 40 የነሐስ)፤ ጃማይካ 110 ሜዳሊያዎች (31 የወርቅ፤ 44 የብርና 35 የነሐስ)፤ ታላቋ ብሪታኒያ 89 ሜዳሊያዎች (25 የወርቅ፤ 30 የብርና 34 የነሐስ)፤ ሶቭዬት ህብረት 77 ሜዳሊያዎች (22 የወርቅ፤ 27 የብርና 28 የነሐስ) እንዲሁም ኢትዮጵያ 72 ሜዳሊያዎች (25 የወርቅ፤ ቦልትን ያክል በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በርካታ ሜዳሊያዎችን የሰበሰበ አትሌት የለም። ቦልት አስራ አንድ የወርቅና ሁለት የብር በማጥለቅ ቀዳሚ ነው። አሜሪካዊው ካርል ሌዊስ ስምንት የወርቅ፤ አንድ የብርና አንድ የነሐስ ሜዳሊያዎች በማጥለቅ ተከታይ ነው። በተመሳሳይ አሜሪካዊው ሚካኤል ጆንሰን ስምንት የወርቅ ሜዳሊያ በማጥለቅ ሦስተኛ ነው። ሌላኛው አሜሪካዊ ላሻውን ሜሪት ስድስት የወርቅና ሁለት የብር ሜዳሊያ በመውሰድ አራተኛ ነው። የረጅም ርቀት ነጉሱ ኃይሌ ገብረስላሴ አራት የወርቅ ሁለት የብርና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ በማጠለቅ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይቀመጣል። የቀድሞ የምርኩዝ ዝላይ ባለ ክብረወሰኑ ዩክሬናዊው ሰርጌ ቡካ ስድስት የወርቅ ሜዳሊያዎችን በዓለም ቻምፒዮና መድረክ በማጥለቅ ኃይሌን ይከተላል። አሜሪካዊው ጃርሚ ዋሪነር አምስት የወርቅና አንድ የብር ሜዳሊያ ይዞ ሰባተኛ ነው። የአስርና አምስት ሺ ሜትር ባለ ክብረወሰኑ ቀነኒሳ በቀለ በአምስት የወርቅና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ ይከተላል። በሴቶች የረጅም ርቀት ንግስቷና የአምስትና22 የብርና 25 የነሐስ) በማስመዝገብ እስከ 7 ያለውን ደረጃ አከታትለው ይዘዋል፡፡ ጃማይካዊው የአጭር ርቀት ንጉስ ዩሴን አስር ሺ ሜትር የዓለም ክበረወሰን ባለቤቷ ጥሩነሽ ዲባባ በዓለም ቻምፒዮና መድረክ አምስት የወርቅ ሜዳሊያ ብታጠልቅም፣ ከአንድ እስከ አስር ባለው ደረጃ ውስጥ አትካተትም። ጃማይካዊቷ ማርሌን ኦቴይ ሦስት የወርቅ፤ አራት የብርና ሰባት የነሐስ ሜዳሊያ በመሰብሰብ በአስራ አራት ሜዳሊያዎች ቀዳሚ ነች። አሜሪካዊቷ አሊሰን ፌሊክስ ስምንት የወርቅ፤ አንድ የብርና አንድ የነሐስ በማጥለቅ በአስር ሜዳሊያዎች ሁለተኛ ነች። ሌላኛዋ አሜሪካዊት ጄርል ሚልስ ክላርክ በአራት ወርቅ፤ ሦስት ብርና ሁለት ነሐስ ትከተላለች። ጃማይካዊቷ ቬሮኒካ ካምቤም ብሮውን ቀጣዩ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ታሪክ በበርካታ ቻምፒዮናዎች ላይ በመካፈል ፖርቹጋላዊቷ የአስርና የሃያ ኪሎ ሜትር ርምጃ ተወዳዳሪ ሰሳን ፌተር እኤአ ከ1991 እስከ 2011 ድረስ በአስራ አንድ ቻምፒዮናዎች በመሳተፍ ትልቅ ታሪክ አላት። ስፔናዊው የሃምሳ ኪሎ ሜትር ርምጃ ተወዳዳሪ ጂሰስ ኤንጅል ጋርሺያም እኤአ ከ1993 እስከ 2013 ድረስ በአስራ አንድ ቻምፒዮናዎች በመካፈል ተመሳሳይ ታሪክ አለው።አዲስ ዘመን የካቲት 7/2011ቦጋለ አበበ", "passage_id": "06685c2154b650e4de54c7efb313a9b9" }, { "passage": "የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ሲቃረብ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቻምፒዮናው ተወዳዳሪ የሚሆኑበትን የሰዓት መስፈርት (ሚኒማ) ለማሟላት በኔዘርላንድ አገር ሄንግሎ ከተማ የሚያደርጉት የማጣሪያ ውድድር ተጠባቂ ነው። ውድድሩ በዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች የሚመረጡበት እንደመሆኑ የአንድ አገር አትሌቶች እርስበርስ የሚያደርጉት ፉክክር ተጠባቂ ነው። በተለይም በዓለም ላይ ውድድር እየጠፋበት በሚገኘው 10 ሺ ሜትር በሁለቱም ፆታ የሚደረጉ ፉክክሮች የሚጠበቁ ናቸው። ከሁለት ወራት በኋላ በኳታር ዶሃ በሚካሄደው የዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አገራቸውን ለመወከልና ሚኒማ ለማሟላት ባለፈው ረቡዕ ምሽት እንደተለመደው ሄንግሎ ላይ ተሰባስበዋል። ባለፉት ሦስት የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናዎች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በ10 ሺ ሜትር የነበራቸውን ክብር ለእንግሊዛዊው አትሌት ሞሐመድ ፋራህ አሳልፈው የሰጡ ሲሆን ፋራህ ካፈው የለንደን አትሌቲክስ ቻምፒዮና ወዲህ ራሱን ከውድድር ማግለሉን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ዳግም ዙፋኑን ለመያዝ ተጠባቂ ናቸው። የትኛው አትሌት የዙፋኑ ተረካቢ ይሆናል? የሚለው ጥያቄ ግን የብዙዎች ጉጉት ነው። በሄንግሎው የማጣሪያ ውድድር ስድስት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ርቀቱን ከ27፡00 በታች በማጠናቀቅ የዓመቱን ፈጣን ሰዓቶች ከመቆጣጠራቸው ባሻገር ኢትዮጵያ በዶሃው ቻምፒዮና ጠንካራና ጥልቀት ያለው የቡድን ስብስብ እንደሚኖራት ፍንጭ የሰጠ ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በሄንግሎው ውድድር የመጀመሪያዎቹን ሦስት ደረጃዎች ይዘው ያጠናቀቁትን አትሌቶች በቀጥታ በዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያን እንዲወክሉ ማድረግ አለማድረጉን ይፋ ባያደርግም መሬት ላይ ካሉ እውነታዎች ተነስቶ የትኛው አትሌት ሊመረጥ እንደሚችል ግምቶች እየተቀመጡ ይገኛሉ። ምናልባትም በሄንግሎው ውድድር ከአንድ እስከ ሦስት ያጠናቀቁት አትሌቶች በአምስት ሺ ሜትር ውድድርም ኢትዮጵያን እንደሚወክሉ እርግጠኛ ሆኖ መናገር የሚቻል መሆኑ እነዚህ አትሌቶች በ10 ሺ ሜትር ደርበው ሲሮጡ የውድድር ጫና እንዳይኖርባቸው ፌዴሬሽኑ ሽግሽግ በማድረግ ከሦስተኛ በላይ ያጠናቀቁ አትሌቶችን ምርጫው የሚያደርግበት አጋጣሚ ሊኖር ይችላል። ከሄንግሎው ውድድር ውጤት ባሻገር አትሌቶቹ ከዚህ ቀደም በቅርብ ጊዜያት በነበሯቸው ውጤቶችና ሰዓቶች መሰረት ምርጫ ሊደረግ እንደሚችልም ይጠበቃል። ያም ሆኖ በሄንግሎው ውድድር ቀዳሚ ሆነው ያጠናቀቁት አትሌቶች ብቃትና ከሦስተኛ በላይ ያጠናቀቁ አትሌቶች ለዓለም ቻምፒዮና የመመረጣቸውን ዕድልና ያላቸውን አቅም መመልከቱ አስፈላጊ ይሆናል። ከሦስት ሳምንታት በፊት በስቶክሆልም ዳይመንድ ሊግ ኬንያዊው ሮኔክስ ኪፕሩቶን ተከትሎ ሁለተኛ በመሆን ሲያጠናቅቅ 27፡01፡02 የሆነ ሰዓት ያስመዘገበው አትሌት ሐጎስ ገብረሕይወት ሄንግሎ ላይ 26፡48፡95 በሆነ የዓመቱ ፈጣን ሰዓት ቀዳሚ ሆኖ ማጠናቀቅ ችሏል። ሐጎስ አሁን ካሉት አትሌቶች በተሻለ በኦሊምፒክና በዓለም ቻምፒዮና በአምስት ሺ ሜትር ብዙ ልምድና ሜዳሊያዎች ያሉት ሲሆን በዘንድሮው ዓመት አምስት ሺ ሜትር ላይ ወጣትና ድንቅ አቋም ያላቸው በርካታ አትሌቶች መምጣታቸውን ተከትሎ ሊሆን ይችላል ትኩረቱን በ10 ሺ ሜትር ላይ አድርጓል። ሐጎስ እነዚህ ጠንካራ ተፎካካሪ ወጣቶች በመጡበት ወቅት ርቀቱን ጨምሮ 10 ሺ ሜትር ላይ ትኩረት ማድረጉ ትክክለኛ ውሳኔ ከመሆኑ ባሻገር ውጤታማም እያደረገው እንደሚገኝ የዘንድሮው ዓመት ሁለት የ10 ሺ ሜትር ውድድሮቹን መመልከት በቂ ነው። በሁለቱ ውድድሮች ያስመዘገባቸው ሰዓቶችን በተለይም በሄንግሎ ውድድር ያስመዘገበውን ውጤት በውድድር ዓመቱ የትኛውም አትሌት አለማስመዝገቡ በዚህ ርቀት በየትኛውም መስፈርት ቀዳሚ ተመራጭ ሊያደርገው እንደሚችል መገመት ይቻላል። ሐጎስ በ10 ሺ ሜትር ስኬታማ ከመሆኑ ባሻገር በአምስት ሺ ሜትርም ያለው ስኬት ከሌሎች አትሌቶች የሚያንስ አይደለም። ምናልባት ግን ፌዴሬሽኑ ከ10 ሺ ሜትር በበለጠ አምስት ሺ ሜትር ላይ በርካታ አማራጮች ስላሉት ሐጎስ 10 ሺ ሜትር ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ እንዲሠራ ማድረግ ከቻለ የብልህ ውሳኔ ወስኗል። ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተለይም በአምስት ሺ ሜትር በዓለም ቁንጮ ከሚባሉ አትሌቶች ተርታ ራሱን ማሰለፍ ችሏል። ሰለሞን በዘንድሮው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ10 ሺ ሜትር ማሸነፉ የሚታወስ ሲሆን በሄንግሎው ውድድር 26:49.46 በማስመዝገብ ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል። 10 ሺ ሜትር ከአምስት ሺ ሜትር የበለጠ ፅናትና ጥንካሬ የሚፈልግ ውድድር እንደመሆኑ ሰለሞን በሄንግሎው ፉክክር ፈጣን ሰዓት ቢያስመዘግብም በርቀቱ ብዙ ልምድ ካለማካበቱ ጋር በተያያዘ ትኩረቱን አምስት ሺ ሜትር ላይ ቢያደርግ የሚመረጥ መሆኑን የስፖርት ባለሙያዎች ይመክራሉ። እርግጥ ነው አንድ አትሌት አምስትም አስርም ሺ ሜትር ደርቦ ቢወዳደር ችግር ላይኖረው ይችላል። ይሁን እንጂ አንዱ ርቀት ላይ ወይም የበለጠ ውጤታማ የሆነበት ርቀት ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ ቢሠራ የበለጠ ውጤታማነቱ እንደሚጎላ እውን ነው። ከሰለሞን ባረጋ ጋር በተመሳሳይ መልኩ ዮሚፍ ቀጄልቻ በአምስት ሺ ሜትር ያለው አቅምና ስኬታ የሚያስቀና ነው። ዮሚፍ አስር ሺ ሜትርን ሲሮጥ የሄንግሎው ውድድር የመጀመሪያው ነው። ያም ሆኖ ድንቅ የሩጫ ተሰጥኦና ቁመና የታደለው ወጣት አትሌት ሐጎስና ሰለሞንን ተከትሎ እንደ መጀመሪያ ውድድር ያስመዘገበው 26:49.99 ሰዓት ሳይደነቅ የሚታለፍ አይደለም። እንደ ሰለሞን ሁሉ ዮሚፍ በርቀቱ ልምድና የተሻለ ችሎታ ይዘው በሄንግሎው ውድድር ላልቀናቸው አትሌቶች ቦታ ለቆ አምስት ሺ ሜትር ላይ ትኩረቱን ቢያደርግ የተሻለ እንደሚሆን ይታመናል። ይህም የአምስት ሺ ሜትር ስብስቡን በደንብ ከማጠናከር ባሻገር 10 ሺ ሜትሩን የበለጠ ልምድ ባላቸው አትሌቶች ስብስብ አስፈሪ እንዲሆን ዕድል ይሰጠዋል። ሐጎስ ገብረሕይወት 10 ሺ ሜትር ላይ መመረጡ አይቀሬ ከሆነ ፌዴሬሽኑ ሽግሽግ ሊያደርግ የሚችለው ወይንም በዚህ ርቀት ትክክለኛውን አትሌት ለመምረጥ የሚጨነቀው በቀሪዎቹ ሁለት ኮታዎች ላይ ይሆናል። ይህም ምርጫ ሰለሞንና ዮሚፍን ደርበው እንዲሮጡ ማድረግ ወይም 10 ሺ ሜትር ላይ ሌሎች አማራጮችን መፈለግ ነው። በዚህ አማራች ውስጥ ሁለት አትሌቶች ወደ 10 ሺ ሜትር የመምጣት ዕድል ሊኖራቸው ይችላል። አንደኛው አትሌት አንዱአምላክ በልሁ ሲሆን 10 ሺ ሜትር ላይ የተሻለ ልምድ አለው። በዚህ ዓመት የኒውዴልሂ ግማሽ ማራቶንን 59፡18 በሆነ ጥሩ ሰዓት ማሸነፍ የቻለ ሲሆን በኢትዮጵያ ቻምፒዮና ሰለሞን ባረጋን ተከትሎ 28፡25 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል። አንዱአምላክ በሄንግሎው ውድድርም 26፡53፡15 አራተኛ ሆኖ ያጠናቀቀበት ሰዓት በርቀቱ ካለው የተሻለ ልምድ አኳያ ቀድመውት ካጠናቀቁት አትሌቶች ያነሰ አያደርገውም። አንዱአምላክ ሄንግሎ ላይ ከአንድ እስከ ሦስት ያጠናቀቁት አትሌቶች በቀጥታ ቢመረጡ እንኳን ተጠባባቂ ሆኖ መያዙ አይቀርም። ስለዚህ ፌዴሬሽኑ ይህን አትሌት የመምረጥ ሰፊ ዕድል እንዳለው ይታመናል። በሌላ በኩል ሄንግሎ ላይ 26፡54፡39 በማስመዝገብ አምስተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ጀማል ይመር ሐጎስ ስቶክሆልም ላይ ሁለተኛ ሆኖ ባጠናቀቀበት ውድድር ርቀቱን መፈፀም ባይችልም ጥሩ አቅም ያለው አትሌት እንደሆነ ይታወቃል። ጀማል ባለፈው የለንደን የዓለም ቻምፒዮናም በአስር ሺ ሜትር አምስተኛ ደረጃን ይዞ ነበር ያጠናቀቀው። በሴቶች መካከል ሄንግሎ የተደረገው ውድድር እንደ ወንዶቹ በርቀቱ አዳዲስና ወጣት አትሌቶች የታዩበት ሲሆን አስር ያህል አትሌቶች ርቀቱን ከ31፡00 በታች ማጠናቀቅ ችለዋል። በውድድር ዓመቱ በሴቶች 10 ሺ ሜትር ውድድሮች እምብዛም ካለመደረጋቸው ጋር ተያይዞ ፌዴሬሽኑ የሄንግሎው ውድድር ላይ ብቻ ተመስርቶ ለዓለም ቻምፒዮናው ምርጫ የሚያደርግበት ዕድል ሰፊ ይመስላል። ስለዚህ በሴቶች መካከል የሚደረገው የብሔራዊ ቡድን ምርጫ ከውዝግብ ሊያመልጥ ይችላል። በሄንግሎው ውድድር የሁለት ጊዜ የዓለም አገር አቋራጭ የወጣት ሴቶች አሸናፊዋ አትሌት ለተሰንበት ግደይ 30፡37፡89 በሆነ ሰዓት ቀዳሚ ሆና ስታጠናቅቅ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮንና የርቀቱ የዓለም ክብረወሰን ባለቤት ነፃነት ጉደታ 30:40.85 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ሆና ፈፅማለች። የ2015 የዓለም ቻምፒዮና የአምስት ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊዋ አትሌት ሰንበሬ ተፈሪ 30:45.14 በመግባት ሦስተኛ፣ ዘይነባ ይመር በ30:46.24 አራተኛ፣ዴራ ዲዳ በ30:51.86 ሰዓት አምስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።ከእነዚህ አትሌቶች መካከል ከአንድ እስከ ሦስት ባለው ደረጃ ውስጥ ያጠናቀቁት አትሌቶች አስር ሺ ሜትር ላይ በውድድር ዓመቱ ሌላ ሰዓት ማስመዝገባቸው ወይም መሮጣቸውን የሚያሳይ መረጃ የለም። ስለዚህ በሄንግሎው ውጤታቸው መሰረት በቀዳሚነት ተመራጭ የሚሆኑበት ዕድል ይኖራል ተብሎ ይጠበቃል። ምናልባት እዚህ ጋር ፌዴሬሽኑ ከ10 ሺ ሜትር ጋር ተቀራራቢ የሆኑ እንደ ግማሽ ማራቶንና አስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድሮች ውጤታቸውን ተመልክቶ በመምረጫ መስፈርቱ ውስጥ ሊያካትት የሚችልበት አጋጣሚ ሊፈጠር እንደሚችልም ማሰቡ አይከፋም። የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮኗ የ10 ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው አትሌት አልማዝ አያና ከአንድ ዓመት በላይ በጉዳት ከውድድር ርቃ መቆየቷ ይታወቃል። አልማዝ ከጉዳት አገግማ ከወር በፊት ከምትታወቅበት ርቀት በተለየ ራባት ዳይመንድ ሊግ ላይ በሦስት ሺ ሜትር ተወዳድራ ስኬታማ መሆን አልቻለችም። ምናልባት አልማዝ ከጉዳቷ አገግማ ለዶሃው የዓለም ቻምፒዮና ትደርሳለች የሚለው የስፖርት ቤተሰቡ ስጋት ነው። አልማዝ ከጉዳቷ ማገገም ከቻለች በዓለም ቻምፒዮና ሚኒማ ሳታሟላና ሄንግሎ ላይ ከተወዳደሩት አትሌቶች ጋር ፉክክር ውስጥ ሳትገባ ያለፈው የዓለም ቻምፒዮና አሸናፊ በመሆኗ በቀጥታ የመወዳደር ዕድል ይኖራታል። ይህም ኢትዮጵያ በዶሃው ቻምፒዮና በ10 ሺ ሜትር ሴቶች በአራት አትሌቶች እንድትወከል ያስችላታል። አዲስ ዘመን ሀምሌ 13/2011 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "52f89b24f4f0bb67a97cc080db22fd07" } ]