query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
2
300
passage
stringlengths
78
8.98k
category
stringclasses
7 values
link
stringlengths
28
740
⌀
negative_passages
listlengths
5
5
142df6b666e72843b7fbbbdab92690bd
9451fdd8f47dc4441314b6ee4fe1c003
የከዋክብቶች አርዓያው ኮከብ አሳዛኝ መጨረሻ
ዓለማችን በታሪኳ ካየቻቸው የቅርጫት ኳስ ከዋክብቶች መካከል በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ከስፖርቱ ዓለም ስኬቱ ባሻገር በተለያዩ ታላላቅ መድረኮች የሚያደርጋቸው አነቃቂ ንግግሮች ተወዳጅነትን ከማፍራት ባሻገር ለበርካታ የዓለማችን ወጣቶች አርዓያ መሆን ችሏል። ከቅርጫት ኳስ አፍቃሪዎች አልፎም ተፅዕኖው በሌሎች ስፖርተኞችና ከስፖርቱ ዓለም ውጪ ባሉ ወጣቶች ላይ ማረፍ ችሏል። ለዓለማችን በርካታ ከዋክብት ስፖርተኞች የአሸናፊነትና ጥሩ ምግባር አርዓያ የሆነው ኮከብ የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ኮቤ ቢን ብርያንት ባለፈው ሳምንት በድንገተኛ የሄልኮፕተር መከስከስ አደጋ ሕይወቱ ማለፉ የስፖርት ቤተሰቡን ቢያስደነግጥም አመለ ሸጋው ኮከብ ወደ ፊትም ሲታወስ ይኖራል። ኮቢ ብራይንት እ.ኤ.አ በ1978 በፊላዴልፊያ የተወለደ ሲሆን ወላጅ አባቱ ጆኢ ብራይንት የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ነበር። ኮቢ ማለት በጃፓን ተወዳጅ የስጋ ምግብ ነው። ይህም የቅርጫት ኳስ ፈርጥ ስሙን ከዚሁ አግኝቷል። 1 ሜትር ከ98 ሴንቲ ሜትር የሚረዝው ኮቢ ብራያንት 96 ኪሎ ግራም ይመዝናል። የ41 ዓመቱ ኮቢ አምስት ጊዜ የኤን ቢ ኤ ቻምፒዮን በመሆን በቅርጫት ኳስ ታሪክ ትልቅ ስምና ዝና ማትረፍ ችሏል። በ 20 ዓመት የቅርጫት ኳስ ፕሮፌሽናል ህይወቱ አያሌ ክብሮችን የጨበጠው ኮቢ ሁለት ጊዜ የኦሊምፒክ ቻምፒወን ሲሆን በ 2008 በመድረኩ ውዱ ተጫዋች መሆን ከመቻሉም በተጨማሪ 2006 ላይ ከቶሮንቶ ራፕቶርስ ጋር በገጠመበት ጨዋታ 81 ቅርጫቶችን በማስቆጠር 2ኛው የምንጊዜም ከፍተኛ ቅርጫት አስቆጣሪ ሆኖ በታሪክ ተመዝግቧል። የሀብት መጠኑ እስከ 650 ሚሊየን ዶላር የሚገመተው ኮቢ ብራያንት ለበርካታ ክዋክብት ስፖርተኞች እውነተኛ አርዓያ በመሆን መነሳሳትን የፈጠረ ታሪክ አኑሮ በካሊፎርንያ በደረሰው የሄሊኮፕተር መከስከስ አደጋ በ 41 ዓመቱ ህይወቱ አልፏል። ሁነቱን አስከፊ የሚያደርገው ደግሞ በአደጋው ወደፊት የአባቷን ሌጋሲ ለማስቀጠል ተስፋ የተጣለባት የ 13 ዓመቷ ጂያና ብራያንት ከአባቷ ጋር ህይወቷ ማለፉ ነው። ሌሎች ሰባት ሰዎችም በአደጋው ህይወታቸው አልፏል። የ 13 ዓመቷ ታዳጊ ጂያና ለመምባ ስፖርትስ አካዳሚ እየተጫወተች የምትገኝ ሲሆን በታሪካዊው የቅርጫት ኳስ ባለሟል በሆነው አባቷ እየሰለጠነች ጨዋታዋን ለማከናወን አገር አማን ብላ እየበረረች ባለበት ሰዓት ያልታሰበውና የሚሊዮኖችን ልብ የሰበረው የእርሷንና አባቷን ህይወት የቀጠፈው መሪር አደጋ ተከሰተ። ከ 4ቱ ልጆች 2ኛ የሆነችው ጂያና ፈጣን ፣ ቀልጣፋና ለቅርጫት ኳስ ጥልቅ ፍቅር የነበራት ሲሆን ከአባቷ የወረስችው እምቅ የክህሎት ሀብት ወደፊት የአባቷን ሌጋሲ ከማስቀጠልም ባለፈ ለቅርጫት ኳሱ አዲስ አብዮት እንደምታመጣ በርካቶች አመኔታ ጥለውባት ነበር። ለስፖርት የተጻፈን የፍቅር ደብዳቤ የሚተርክ 5 ደቂቃ የሚቆይ የአንሜሽን ፊልሙ በ 2018 ታላቁን የኦስካር ሽልማት አሸናፊ ያደረገው ኮቢ ብራያንት ከውድ ልጁ ጋር ወደ ማይመለስበት ዓለም ለመሄድ ተገዷል። የኮቢ ብራይንት ህልፈት የዘንድሮውን 62ኛውን የግራሚ ሽልማት ላይ የኀዘን ድባብ የፈጠረ ሲሆን የመድረኩ መሪ የሆነችው አሊሻ ኪስ መታሰቢያነቱ ‹‹ለእርሱ ይሁን›› ብላለች። ‹‹ከደቂቃዎች በፊት ሎስ አንጀለስ ፣ አሜሪካና መላው ዓለም ጀግናውን ተነጠቀ። ኮቢ ብራያንት የተለየና ለሚሊዮኖች መነሳሳትን የፈጠረ ዘመን ተሻጋሪ ነው። በሆነው ነገር ልባችን ክፉኛ ተሰብሯል›› ስትልም ታሪካዊውን የቅርጫት ኳስ ባለሟል አስባለች። በሎስ አንጀለስ ሌከርስ የክለብ ቆይታው 5 ጊዜ ቻምፒወን የሆነው ኮቢ ብራያንት ህልፈቱ ከተሰማ በኋላ በአሜሪካ የተሰናዱት ዝግጅቶች በታላቅ ክብር አስበውታል። የቅርጫት ኳስ ጨዋታዎች ሲከናወኑ አባታቸውን በማሰብ ለደቂቃ የቆየ የህሌና ጸሎት አድርገዋል። የእግር ኳሱ ዓለም ኮከቦችና ዝነኛ ክለቦች በኮቢ ብራያንት ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ከመግለፅ ወደ ኋላ አላሉም። ብራዚላዊው ኮከብ ኔይማር ጁኒየር ከሊል ጋር በተደረገው ጨዋታ 2 ጎሎችን ያስቆጠረ ሲሆን 2ኛውን ጎል መታሰቢያነቱ ለኮቢ ብራያንት አድርጓል። ቄንጠኛው ተጫዋች የእጆቹን ጣቶች ወደ ሰማይ ከፍ በማድረግም ኮቢ ብራያንትን በልዩነት አስቧል። ‹‹በመልካም ስነምግባር የታነጸው የአሸናፊነት መንፈስህ አሁን ላለሁበት ጥሩ ደረጃ መሰረት ሆኖኛል። አንተ ሁልጊዜም ለየት ያለ ማንነትን በመላበስ ነገን ለሚኖሩ ተምሳሌት ሆነሃል ፣ ጥለኸን በመሄድህ ልቤ በኀዘን ተሰብሯል፣ እጅግ በጣም እወድዳለሁ›› ሲል ቤልጄማዊው አጥቂ ሮሜሉ ሉካኩ የህይወት ምሳሌው ስለነበረው ኮቢ ብራያንት ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን ገልጿል። በቅርጫት ኳስ ሜዳ ላይም ሆነ ከሜዳ ውጪ ለሁሉም ስፖርተኞች እውነተኛ ምሳሌ መሆኑን የጠቀሰው የባርሴሎና እግር ኳስ ክለብ ‹‹በሆነው ነገር አዝነናል ለቤተሰቦችህና በአጠቃላይ ለሚወዱህ መጽናናትን ከልብ እንመኛለን›› ሲልም ባርሰሎና እንደ ክለብ ተመኝቷል። ፖርቱጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በተፈጠረው ነገር መደናገጡን ገልጾ ‹‹ኮቢ ብራያንት ለበርካቶች አርዓያ የሆነ›› ሲልም አክሏል። ሮናልዶ ቀጥሎም ለቤተሰቦቹና በአደጋው ጉዳት ለደረሰባቸው ሁሉም ቤተሰቦች መጽናናትን ከልብ ተመኝቷል። ኤሲ ሚላን ‹‹ጨለማውን ክስተት ለመግለጽ ቃላቶች የሉንም ፣ በስፖርቱ ዘመን ተሻጋሪ ከሆኑ ጀግኖች ዋና ተዋናዩን አጥተናል። ስላበረከትከው እጹብ ድንቅ ነገር እና ስለደገፍከን ልባዊ ምስጋናችን በአለህበት ይድረስ፣ ስለ እውነት ሁላችንም ተደናግጠናል ሲል ደጋፊው ስለነበረው ኮቢ ኀዘኑን ገልጿል። ‹‹ለዚህ ትውልድ ትልቅ ተምሳሌት በመሆን ለበርካቶች በተስፋ ውስጥ መልካም ህይወት እንዳለ መምህር ሆነሃቸዋል። ለነብስህ ፍጹም ሰላምን ይስጣት›› አንድሪያ ፒርሎ የተመኘው ልባዊ የኀዘን ምኞት ነው።አዲስ ዘመን ጥር 24/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=26562
[ { "passage": "ባለፈው ዓመት የታንዛኒያው ሲምባን በመልቀቅ ወደ ጅማ አባ ጅፋር ያመራው ዳንኤል አጃዬ በዓምና ቆይታው ድንቅ ጊዜ በማሳለፍ በሊጉ ዝቅተኛ ጎል የተቆጠረበት ግብ ጠባቂ መሆን ሲችል ከቡድኑ ጋር የፕሪምየር ሊግ ቻምፒዮን፣ በግሉ ደግሞ ኮከብ ግብ ጠባቂ ሆኖ አጠናቋል።ዘንድሮ ክለቡ በአምናው ወጥ አቋም እና ውጤታማነት ላይ ባይገኝም የ29 ዓመቱ ጋናዊ ዘንድሮም በጥሩ ብቃቱ ላይ ይገኛል። በሁለተኛው ዙር ሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ግብ ሳያስተናግድ በመውጣትም በወቅታዊ ድንቅ አቋም ላይ ይገኛል።በሀገሩ ክለቦች ሊበርቲ ፕሮፌሽናልስ እና ሚዴአማ፣ በደቡብ አፍሪካው ፍሪ ስቴት ስታርስ እና በታንዛኒያው ሲምባ ተጫውቶ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ዳንኤል አጄይ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ባደረገው አጠር ያለ ቆይታ በእግርኳስ ህይወት ጉዞው፣ በተለያዩ ጊዜያት ከጨዋታ ስላራቀው የግል ጉዳይ እና ስለ ኢትዮጵያ እግርኳስ አስተያየቱን ሰጥቷል።የእግርኳስ ጅማሮህ ድንቅ ነበር። የ2009 የዓለም ከ20 ዓመት በታች ዋንጫ ስታነሳ ከነ አንድሬ አዬው፣ ጆናታን ሜንሳህ እና ዶሚኒክ ኤዴህ ጋር የቡድኑ ወሳኝ ተጫዋች ነበርክ። የ2010 አፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ ድረስ የተጓዘው የጋና ስብስብም አካል ነበርክ… ከዚህ አጀማመር ያልቀጠልክበት ምክንያት ምንድነው?በእኔ አመለካከት በ2009 ከኛ በፊት የትኛውም የአፍሪካ ሀገር ያላሳካውን የዓለም የ20 ዓመት በታች ዋንጫ አሸናፊ ከነበርን በኋላም የነበረው ጊዜ በትክክል ጥሩ እና ወጥ ነበር። በአፍሪካ ዋንጫ በአንጎላ አዘጋጅነት በተደረገው ላይ ከግብፅ ብሄራዊ ቡድን ጋር ለፍፃሜ የደረሰው የቡድኑ አባል ነበርኩ፣ ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ጋቦን ባዘጋጁት ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ላይም ተሳታፊ ነበርኩ፣ የ2010 የደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ አምልጦኛል፣ በ2011 የመላው አፍሪካ ውድድሮች ማፑቶ ላይ በጋና ታሪክ በውድድሩ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ ከነበረው የቡድኑ አካል ነበርኩ። በተጨማሪም ጅማ አባጅፋር ወደ ፕሪምየር ሊጉ ባደገበት ዓመት የፕሪምየር ሊጉ አሸናፊ በሆነው ቡድን ውስጥ የቡድኑ አባልና የታሪኩም አካል ነኝ። አባጅፋርን በተቀላቀልኩበት ዓመት ውጤታማ ነበርኩ፤ በሊጉ አነስተኛ ግብ የተቆጠረብኝ በአንድ ጨዋታ ከሁለት ግብ በላይ አልተቆጠረብኝም። ከዚህም በላይ ለመስራት ክለቤንና ቤተሰቤን ለመርዳት ጠንክሬ እየሰራሁ እገኛለሁ።ከጋና ወደ ደቡብ አፍሪካ፤ ቀጥሎም ወደ ታንዛንያ አሁን ኢትዮጵያ… የእስካሁኑ የእግርኳስ ጉዞህስ በጠበቅከው መልኩ እየተጓዘ ነው?ሰዎች ወደ አውሮፓ ወይም ወደ ሌሎች ሀገራት ሄደህ ለምን አትጫወትም ይሉኛል። ነገር ግን እዚህ ባለው ነገር ደስተኛ ነኝ። አዳዲስ ነገሮችን እያወቅኩ ነው። በአሰልጣኞቼ እና እዚህ ባለው ነገር ደስተኛ ነኝ፡፡ የትም ብትሄድ ለመማርና አዳዲስ ነገሮችን ዝግጁ መሆን አለብህ፤ ወደ ኢትዮጵያ ስመጣ ብዙዎች ተቃውመውኝ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ምርጫዬ ትክክል ነበር፡፡ኢትዮጵያ ጥሩ የእግርኳስ ሀገር ናት፤ ብዙ ባለ ተሰጥኦ ተጫዋቾች አሏት። በብሄራዊ ቡድናችሁም ሙሉ ለሙሉ በሀገራችሁ ዜጎች ነው የምትጠቀሙት። ብዙ የዓለማችን ሀገራት የሌላ ሀገር ዜግነት ያላቸውን ተጫዋቾች ለብሄራዊ ቡድናቸው ሲያጫውቱ እንመለከታለን። በኢትዮጵያ ግን በብሄራዊ ቡድኑ የኢትዮጵያውያን ብቻ ናቸው የሚጫወቱት። ለሀገራችሁ ተጫዋቾች ያላችሁን እምነት በእያንዳንዱ ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያውያንን በመጠቀም ታሳያላችሁ። ሌሎች ሀገሮች የሀገራቸውን ተወላጆች ላይ እምነት የላቸውም። ሀገሬን ጋና ጨምሮ ሌሎች ሀገራት እንደዚህ አይደለም፤ አቋራጭን ነው የምንጠቀመው። ለዚህም ነው ኢትዮጵያ የእግርኳስ ሀገር ናት ያልኩት። በአጠቃላይ እዚህ የመጣሁት ዋንጫዎችን ለማንሳትና አዳዲስ ፈተናዎችን ለመጋፈጥ ነው።አምና በጅማ ድንቅ ጊዜ ከማሳለፍህ በተጨማሪ የሊጉ ዝቅተኛ ጎል የተቆጠረበት ግብ ጠባቂ ነበርክ… የዘንድሮው አቋምህ ባንተ እይታ ምን ይመስላል?እስካሁን 15 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፌ 7 ግብ ብቻ ነው የተቆጠረብኝ። በሀዋሳ 3፤ በቅዱስ ጊዮርጊስ 2 እና በመቐለ 2 ግቦች ናቸው የተቆጠሩብኝ። እነዚህም ግቦች ከሜዳችን ውጭ የቆጠሩብኝ ናቸው። በሜዳችን ባደረግናቸው ጨዋታዎች ምንም ግብ አላስተናገድኩም። በእርግጥ እኔ ባልነበርኩባቸው ጨዋታዎች ላይ በደቡብ ፖሊስ 6 በድሬዳዋ በሜዳችን 3 ግብ አስተናግደናል። ከተመለስኩ በኋላ ግን ተስተካክሏል። ለዘጠኝ ጨዋታዎችም ግብ አልተቆጠረብኝም። ስለዚህ በዚህ የውድድር ዓመት ለእኔ ጥሩ ነው ማለት እችላለሁ፡፡ዘንድሮ በግልህ ጥሩ ብትሆንም ቡድኑ በሜዳ ላይ እየተቸገረ ነው። ይህን እንዴት ታየዋለህ?ባለፈው ዓመት አብረውን ከነበሩት ተጫዋቾች በአብዛኛዎቹ ለቀዋል። አሁን ያሉት አዳዲስ ተጫዋቾች ከባለፈው ዓመቶቹ ብስለትና ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ናቸው። ነገር ግን የሊጉ ቻምፒዮን መሆናችን ትኩረት እድንስብ አድርጎናል። ሁሉም ቡድን እኛኝ ለመግጠም በተለየ ትኩረትና ዝግጅት ነው የሚያደርጉት። ይህ ደግሞ ጨዋታዎችን ያከብድብናል። እንደዛም ሆኖ እንደባለፈው ዓመት ባይሆንም በግብ ክፍያ ተበልጠን 7 ጀረጃ ላይ ነው ያለነው። ደረጃችንን ለማሳደግ እና ለሁለት ተከታታይ ዓመታት የሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ከተጫዋቾች ከቡድኑ አመራሮች ጋር ጠንክረን እየሰራን ነው፡፡አምናም ሆነ ዘንድሮ በግል ጉዳይ ወሳኝ ጨዋታዎች አልፈውሀል። የግል ጉዳዩ ምንድነው? ይህ በእግርኳስ ህይወትህ ላይ ተፅዕኖ ፈጥሮብሀል?ባሳለፍነው ዓመት ዘንድሮም የተወሰኑ ጨዋታዎች አምልጠውኛል። የግል ጉዳዬ ስለሆኑ መናገር አልፈልግም፤ ምክንንያቱም ሰዎች የግል ጉዳዮቼን እያነሱ ጫና እዲያደርጉብኝ እና ተፅዕኖ ውስጥ እንዲከቱኝ አልፈልግም። ወደ ጅማ አባጅፋር ከመምጣቴ በፊት ያለብኝን ጉዳይ አስረድቼ ፍቃድ እንደሚሰጡኝ ከተስማማን በኋላ ነው የፈረምኩት እንጂ በድንገት የተከሰተ ነገር አይደለም። በዚህ አጋጣሚ ላመሰግናቸው እወዳለሁ። በሚቀጥለው ዓመት ጉዳዬ መቋጫ ያገኛል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። በጅማ አባ ጅፋርም ቆየሁ፤ ወደ ሌላ ክለብም ሄድኩ ሙሉ ትኩረቴ ጨዋታ ላይ ነው እንዲሆን የምፈልገው። ምናልባት ልጄ ካልታመመችብኝ ወይም ሌላ ድንገተኛ ነገር ካልገጠመኝ በስተቀር መጓዝን አልፈልግም።ሊጋችን በውጪ ጎል ጠባቂዎች እየተጨናነቀ ነው። የዚህ ምክንያቱ ምን ይመስልሀል? የአመለካከት ችግር ነው ወይስ በጉልህ የሚታይ የችሎታ ልዩነት አለ?በእግሊዝ በስፔን በተለያዩ የዓለም ሀገራት ሊጎች ውስጥ ብዙ የውጭ ሀገር ግብ ጠባቂዎች አሉ። ይህ መሆኑ የሀገሬው ግብ ጠባቂዎች ከውጪዎቹ ብዙ የሚማሩት ነገር አለ። ዋናው ነገር ለመማር ፈቃደኛ መሆን ነው። እኔ በግሌ ፕሮፍይሌ ትልቅ ነው ብዬ ወደ የኢትዮጵያ ሄጄ አልጫወትም አላልኩም። እዚህ ከመጣው በኋላ እዚህ ካሉ አሰልጣኞቼ ብዙ የተማርኳቸው ነገሮች አሉ። ዋናው ነገር አዳዲስ ነገሮችን ለማወቅ ራስን ዝግጁ ማድረግ ነው። ተሽሎ ለመገኘት ጠንክሮ መስራት ነው።", "passage_id": "1182a37d1f7d3c82c1d3fb9bdcd199ef" }, { "passage": "መጀመርያውንም መጨረሻውንም አንድ ክለብ ብቻ በማድረግ ወጥ በሆነ አቋም ለአስራ አምስት ዓመታት አገልግሏል። በቁመት አጭር ከሚባሉ አጥቂዎች መካከል ቢመደብም በቅልጥፍናው እና በፍጥነቱ ጎል በማስቆጠር አቅሙ ይታወቃል። ይህ የዘጠናዎቹ ድንቅ አጥቂ አሸናፊ ሲሳይ (አሹ) ማነው ?በዛን ዘመን የተጫዋች ምልመላ ባልነበረበት ጊዜ የክለቡ የልብ ደጋፊና ሥራ አስኪያጅ በመሆን ቅዱስ ጊዮርጊስን ያገለገሉት አደበተ ርዕቱሁ አንጋፋው የቀለም መምህር ጋሽ ታደሰ መሸሻ በሚያስተምሩበት ተፈሪ መኮንን የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ሆኖ አንድ ብላቴና ይመጣል። ሁሌም በእረፍት ሰዓት ጨዋታ የሚያዘወትረው ይህ ታዳጊ በአንድ ቀን ጋሽ ታዴ አይን ውስጥ ይገባል። የኳስ አያያዙ፣ ቅልጥፍናው፣ ፍጥነቱ አስገርሟቸው ለባልንጀራቸው ለአባቱ እንዲህ ይላሉ “ይሄ ልጅ ጥሩ የእግርኳስ ችሎታ አለው። ለቅዱስ ጊዮርጊስ እንዲጫወት ይዤው ልሂድ ? ማን ያውቃል በዚህ ታላቅ ክለብ ውስጥ ኮከብ ተጫዋች ይሆን ይሆናል።” አቶ ሲሳይም ይፈቅዱና ጋሽ ታዴ ኮንትራት ታክሲ ይዘው ሳር ቤት (ብስራተ ገብርኤል) ሜዳ ይወስዱታል። እንዳጋጣሚ ሆኖ ሜዳው ይያዝባቸው እና ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አካባቢ በሚገኝ ሜዳ በድጋሚ ይዘውት ይሄዳሉ። የወቅቱ የታዳጊ ቡድኑ አሰልጣኝ እንዳልክ ነጋ (በህይወት የለም)። ያን ትንሽ ልጅ አይቶ ለጋሽ ታዴ እንዲህ አላቸው። ” ጋሽ ታዴ ይሄ ልጅ ህፃን ነው። ለ” ሲ” ቡድን ለመጫወት አልደረሰም። ለማንኛውም ይግባና ልየው።” ይላቸዋል። በል ልብስህን አውልቅ ማልያ ልበስ ብለውት ልብሱን ሲያወልቅ ጋሽ ታዴ ደነገጡ። ምክንያቱም ልብስ ለብሶ ሲያዩት ቀጭን፣ ሰውነት የሌለው ይመስላል። ሆኖም ግን በጣም ጠቅጠቅ ያለ ሞላ ያለ ሰውነት ያለው ጠንካራ ሆኖ ያገኙታል። በዚህ ተገርመው የሙከራው ጊዜው ደርሶ ወደ ሜዳ ይገባና መጫወት ይጀምራል። ለጊዜው ሜዳ ገብቶ ኳሱን ለማግኘት ቢቸገርም አጋጣሚ ሆኖ መጀመርያ ያገኘውን ኳስ በደረቱ አብርዶ በሁለት ጉልበቱ አውርዶ አስገራሚ ሁኔታ ጎል ያስቆጥራል። ይህን ያየው አሰልጣኝ በጣም ተገርሞ ለተጨማሪ ቀን ቢቀጥረውም ሙከራውን በስኬት አጠናቆ መጀመርያውም መጨረሻውም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊሆን በዛው ይቀራል። ይህ ታናሽ ብላቴና የዛሬ ባለታሪካችን የዘጠናዎቹ ኮለብ አሸናፊ ሲሳይ ይባላል። ተወልዶ ያደገው ተፈሪ መኮንን ት/ቤት አካባቢ ነው። ከላይ በገለፅነው አጋጣሚ በ1981 የቅዱስ ጊዮርጊስ “ሲ” ቡድንን በመቀላቀል የእግርኳስ ህይወቱን ይጀምራል። ከሦስት ዓመት የታዳጊ ቡድን ቆይታ በኃላ ቅዱስ ጊዮርጊስ አብዛኛው ተጫዋቾቹን ለብሔራዊ ቡድን በማስመረጡ ምክንያት የተገኘውን አጋጣሚ በመጠቀም በ1984 ወደ ዋናው ቡድን ማደግ ችሏል። በዋናው ቡድን ኢትዮጵያ መድን ላይ ጎል በማስቆጠር የጎል አካውንቱን የከፈተው ይህ የጎል አዳኝ ከዚህ በኃላ የሚያቆመው ጠፍቶ በደጋፊዎቹ እየተወደደ ህልሙን መኖር ይጀምራል።በብሔራዊ ቡድን አብሮት የተጫወተው ድንቁ አማካይ አንዋር ያሲን (ትልቁ) ስለ አሹ ይሄን ምስክርነት ይሰጣል። “አሸናፊ ለተከላካዮች የማይመች ነው። አሸናፊ ሜዳ ውስጥ አለ ከተባለ ተከላካዮች ሠላማቸውን ያጣሉ ፣ ይረበሻሉ እና መረጋጋት ያቅታቸዋል። የጎል አጋጣሚ ካገኘ የማይምር ነው። ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለረጅም ዓመታት በትልቅ ኃላፊነት አቋሙን ጠብቆ የተጫወተ በጣም የማከብረው ትልቅ ተጫዋች ነው”። ይለዋል።በታዳጊ ቡድን አራት በዋናው ቡድን አስራ አንድ በጥቅሉ ለአስራ አምስት ዓመት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሲጫወት ብዙ ገድሎችን በአስገራሚ ብቃቱ መፈፀም ችሏል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በተከታታይ ሦስት ዓመታት የሀገሪቱን ከፍተኛ ውድድሮች ከ1986–88 ባለው ጊዜ ውስጥ ባሳካቸው የአዲስ አበባ ቻምፒዮን ፣ የኢትዮጵያ ቻምፒዮን፣ የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ድል ውስጥ ትልቅ ሚና ነበረው። በግሉ 1986 ኮከብ ተጫዋች በ1987 ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ በመሆን ክብርን አግኝቷል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በአዲስ አቀራረብ መካሄድ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ደግሞ አራት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን እና በ1991 የፌዴሬሽን የመረጃ አያያዝ ስህተት ቢኖርበትም በመጨረሻም ኮከብ ጎል አስቆጣሪ በመሆን አጠናቋል።የቅዱስ ጊዮርጊስ የረጅም ዓመት ደጋፊ የሆነው ጌዲዮን ስዮም ሲናገር ” አሹ ልባም የሆነ ምርጥ አጥቂ ነው። የተነጠቀውን ኳስ ሳያስጥል የማይቆም ጎል አስቆጣሪ ነው። አመለ ሸጋ በደጋፊ ሁሉ የሚወደድ ነው። አሹ የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫዋች ብቻ ሳይሆን የልብ ደጋፊ የሆነ አጥቂ ነው”። ይለዋል። ብዙ የሚነገሩለት በርካታ ተስዕጦ ያለው ይህ ፈጣን አጥቂ በብሔራዊ ቡድን በታዳጊ፣ በወጣት፣ በኦሊምፒክ ቡድን አንስቶ እስከ ዋናው ቡድን ድረስ በመጫወት ሀገሩንም መጥቀም ችሏል።እስቲ በድጋሚ በወደ ኃላ ልመልሳችሁና ጋሽ ታደሰ መሸሻ እጁን ይዘው የሄዱት ያብላቴና በሚወዱት ክለባቸው የሚወደድ፣ የሚደነቅ እንዲሁም ጎል አስቆጥሮ እራሳቸውን ሳይቀር የሚያስጨፍር ሲሆን ምን እንደሚሰማቸው ወደ ኃላ አስታውሰው እንዲነግሩኝ ጠየኳቸው። (በእንባ እና ሲቃ በተሞላው አንደበት) እንዲህ ብለው ነገሩኝ ” በዛን ጊዜ እኔ አሸናፊ ሲሳይ አይደለም የሚታየኝ። ከልቤ እውነቱን ልንገርህ? ልቤ ሞልቶ በደስታ ተውጬ የምወደው ክለቤ እንደዚህ ዓይነት ማንም ተከላካይ የማያቆመው በፍጥነቱ ጥሶ ገብቶ ጎል ሲያስቆጥር ፣ ኳስ ሲነጠቅ ወደ ኃላ ተመልሶ ሄዶ አስጥሎ ለጓደኞቹ አቀብሎ እራሱ የሚያገባቸው ጎሎች ሳይ እውነት ከምንም በላይ የሚያረካኝ እርሱ ነበር። ከአባቱ ጋር ሁልጊዜ ሜዳ አብረን ነው የምንገባው አሸናፊ ጎል ባገባ ቁጥር ተያይዘን መተቃቃፍ መሳሳም ነበር። ብቻ አሸናፊ ታሪኩ ትንሽ አይደለም ረዥም ነው። እኔ በዚህ ዘመን አሸናፊን የሚመስል ተጫዋች የለም”። በማለት ተናግረዋል።ሌላኛው አብሮት የተጫወተው ድንቁ አማካይ ሙሉዓለም ረጋሳ ስለ አሸነፊ ምስክርነት ሲናገር “ፈጣን፣ ጉልበተኛ እና ታታሪ አንድ አጥቂ ሊያሟላ የሚገባቸውን ነገሮች በሙሉ ያሟላ በድፍረት እና በፍጥነት ሁሉን ነገር ማድረግ የሚችልበት አቅሙ ያለው አጥቂ ነው”። ይለዋል። ይህ ስኬታማ ተጫዋች በ1995 እግርኳስን ካቆመ በኃላ ኑሮውን አሜሪካ ካደረገ አስራ አምስት ዓመት ሆኖታል ሶከር ኢትዮጵያ ካለበት ሀገር አሜሪካ አግኝተዋው አናግራዋለች።“በቅድሚያ እዚህ ፕሮግራም ላይ እንግዳ  አድርጋችሁ ስለጋበዛችሁኝ ከልብ አመሰግናለሁ። እንግዲህ እግርኳስን የጀመርኩትም የጨረስኩትም በጊዮርጊስ ነው። C ቡድን ከገባሁበት ከ1981 ጀምሮ እግርኳስን እስካቆምኩበት 1995 ድረስ ወደ አስራ አምስት ዓመት ቆይታዬም ሁሉ እጅግ በጣም ደስተኛ ነበርኩ። ጥሩ ፍቅር፣ መከባበር እና መተሳሰብ ነበረን። በአጠቃላይ ልዩ ዘመን ነበር። ያ ጊዜ መቼም መቼም ከአዕምሮዬ አይጠፋም። ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ሁሉንም ስኬቶች እንደ ቡድን በግሌም ጭምር አግኝቻለው። ኮከብ ተጫዋች እና ኮከብ ጎል አስቆጣሪ በመሆን ተሸልሜ አለው። በብሄራዊ ቡድን በነበርኩበት ጊዜ በሁሉም የዕድሜ ዕርከን ተመርጬ ሀገሪን በሚገባ አገልግያለው። በዚህም በጣም ጥሩ እና ውጤታማ የነበርኩበትን ጊዜ አሳልፊያለው። በዚህም እንደማንኛውም ተጫዋች ደስተኛ ነበርኩ።“ፈጣሪ ይመስገን ምንም ነገር አይቆጨኝም። ሁሉንም ነገር ከሞላ ጎደል አሳክቻለሁ፣ አግኝቻለሁ፣ አድርጌያለሁ ብዬ ነዉ የማስበው። ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን በጣም ደስተኛ ሆኜ ነው የእግር ኳስ ተጫዋችነት ዘመኔን ያሳለፍኩት። ምንም የምቆጭበት አላሳካሁትም የምለው ነገር የለኝም። ፍጥነቱን ከየት አገኘህው ላልከኝ ያው ቁመቴ አጭር ነው። አጭር ስለሆንኩም ፈጣን እና ቀልጣፋ እንድሆን የረዳኝ መሰለኝ። በተጨማሪ ግን አሰልጣኝ አስራት ኃይሌ የፍጥነት እና የቅልጥፍና ልምምዶችን በተደጋጋሚ ያሰራኝ ስለነበረ ከዛም ያመጣሁት ይሆናል። ሁለቱ ተደማምረው ነው ፍጥነት እና ቅልጥፍናዬን ያሳደጉልኝ።” አቶ ታደሰ መሸሻ የአባቴ የቅርብ ጓደኛ ናቸው።  እሳቸው ናቸው ወደ ጊዮርጊስ C ቡድን ይዘውኝ የመጡት። C ቡድንም ሞክሬ ከዛም አለፍኩ። አቶ ታደሰ ማለት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ጊዜያቸውን እና ጉልበታቸውን ለዚህ ታላቅ ክለብ ያበረከቱ ድንቅ ሰው ናቸው። በተጨማሪም  C እና B ቡድኖችን ከጃን ሜዳ አንስተው እስከ ስታዲየም ድረስ እየሄዱ ያበረታታሉ። ጥሩ ጥሩ ተጫዋቾችንም ወደ ጊዮርጊስ በማምጣት ቡድኑ እንዲጠናከር ያደርጋሉ። እጅግ በጣም ሊመሰገኑ የሚገባቸው ሰው ናቸው። ከዚህም መሀል ብርሃኑ ፈየራን፣ እኔን እና ሌሎችንም ተጫዋቾች አምጥተው ጊዮርጊስን ለማጠናከር ላደረጉት ትልቅ ጥረት ሊደነቅ እና ሊወደስ የሚገባው ነው። እኚህን ታላቅ ሰው በዚህ አጋጣሚ ላመሰግናቸው እወዳለሁ ።“ከሀገር ከወጣሁ አሁን 15 ዓመት ሆኖኛል። የአንድ ሴት ልጅ አባት ነኝ። ወደፊት የሀገሬን ስፖርት ለማገዝ ወይም ደግሞ የአሰልጣኝነት ትምህርት ወስጄ አሰልጣኝ ለመሆን አስባለሁ። እስካሁን ግን ምንም ሀሳብ የለኝም። ወደፊት ከራሴ ጋር ተማክሬ አንድ ነገር እሰራለሁ ብዬ አስባለሁ ።“በመጨረሻም ለቅዱስ ጊዮርጊስ ማደግ ከፍተኛ አስተዋፆኦ በማድረግ ገንዘባቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ጊዜያቸውን ሰውተው ይህን ታላቅ ክለብ ጥሩ ደረጃ እንዲደርስ ካደረጉ ሰዎች መካከል አቶ ዳዊት አሰፋ ፣ ጀማል ፣ ሳህሌ ወልደሰንበት ፣ ግርማ ነዳ እና ሌሎች ጥሩ እና ድንቅ ሰዎች የነበሩበት እና ያሉበት ክለብ ነው። እነዚህን ከልቤ ሳላመሰግናቸው አላልፍም። እናተም ዕድሉን ስለሰጣችሁኝ አመሰግናለው።”* በአሸናፊ ሲሳይ ላይ በፌዴሬሽኑ የመረጃ አሰባሰብ ስህተት ምክንያት በ1991 ስለተፈጠረው ጉዳይ እና ወደ ክስ አምርቶ በጓሮ በር መቋጫ ስላገኘው ነገር የፊታችን ሐሙስ ይዘን የምንቀርብ ይሆናል።", "passage_id": "89031189b831d3009d74d8a38fc2d6d8" }, { "passage": "በኢትዮጵያ እግርኳስ ከታዩ ምርጥ የግራ እግር ተጫዋቾች መካከል አንዱ የነበረው እና በሁሉም ቦታዎች ሲጫወት የምናቀው የቀድሞ የመብራት ኃይል አንበል አፈወርቅ ኪሮስ የ1993ቱ የሦስትዮሽ ዋንጫን ስኬት አስመልክቶ በትውስታ አምዳችን ያስቃኘናል።ለአንድ ክለብ ታማኝ ሆኖ መዝለቅ በማይታሰብበት በዚህ ዘመን ለብዙዎች ምሳሌ መሆን የሚችል የመልከም ስብዕና ባለቤት የሆነው አፈወርቅ ኪሮስ ለመብራት ኃይል ለረጅም ዓመታት በታማኝነት ያገለገለ ታታሪ፣ መሪ፣ ሁለገብ እና ለቡድኑ ያለውን በመስጠት የሚታወቅ ጠንካራ ተጫዋች ነበር። አፈወርቅ ሕይወቱ ከመብራት ኃይል ጋር የተቆራኘው ገና የ11 አመት ታዳጊ ሳለ ነበር፡፡ አባቱ አቶ ኪሮስ የመብራት ኃይል ሠራተኛ የነበሩ በመሆናቸው የሠራተኛ ልጆች የሚጫወቱበት የታዳጊ ፕሮጀክት ሲቋቋም በ1978 በመብራት ኃይል ‹‹D›› ቡድን በመግባት በአንበልነት ቡድኑን ገና በታዳጊነቱ መምራት ችሏል። በዚህ ቡድን መጫወት ጀምሮ ደረጃ በደረጃ ባሳየው ከፍተኛ እድገት በ1985 ዋናውን የመብራት ኃይል ቡድን ተቀላቅሏል፡፡ ከመብራት ኃይል ጋር ብቻ በዘለቀው የ14 ዓመታት የተጫዋችነት ዘመኑ 2 የሊግ፣ 1 የኢትዮጵያ ሻምፒዮና፣ 1 የጥሎማለፍ እንዲሁም 3 የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ከቡድኑ ጋር አንስቷል፡፡ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ከ 1988 እስከ 1995 ድረስ ተጫውቷል፡፡በተለይ እስካሁን ለክለቡ የሰማይ ያህል ርቆበት መድገም ያልቻለው የ1993ቱ የሦስትዮሽ ዋንጫ በመብራት ኃይል እግርኳስ ታሪክ በግንባር ቀደምትነት ተጠቃሽ ከሚሆኑ ስኬቶች ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚወስደው ነው። አፈወርቅ እንደ ተጫዋች ከነበረው አስተዋፅኦ በተጓዳኝ ድርብ ኃላፊነት ይዞ ቡድኑን በአንበልነት በመምራበት የሀገሪቱን ሁሉንም ዋንጫ፤ የስፖርታዊ ጨዋነት ዋንጫንም ጨምሮ ያነሳ ባለ ታሪክም ነው። ኢትዮጵያዊው ማልዲኒ እየተባለ የሚጠራው አፈወርቅ ዳግም ወደ ኃላ አስራ ዘጠኝ ዓመት በትውስታ መልሶን ያኔ የነበረውን ጊዜ አስታውሶ የተፈጠረበት ስሜት ከሚኖርበት አሜሪካ ቺካጎ ከተማ አናግረነው እንዲህ አስታውሶናል።” ሁልጊዜም የምለው ነው። ዘጠና ሦስት ለኔ ትልቅ ቦታ የምሰጠው ዘመን ነው። በኢትዮጵያ የሚገኙ ዋንጫዎችን በጠቅላላ በአንበልነት ማንሳት ለኔ ትልቅ ክብር ነው። ከዚህ በላይ ለኔ ክብር አለ ብዬ አላስብም። ይህን ስልህ ምን ማለቴ ነው። አንድ ሰው ለአንድ ክለብ በታማኝነት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ አገልግሎ ቡድኑ በአንበልነት እየመራ በመጨረሻም በሀገሪቷ ያሉትን ሁሉንም ዋንጫ፣ የፀባይ ዋንጫንም ጨምሮ ጠቅልሎ ማንሳት እና ወደ ቡድንህ ማስገባት ከዚህ በላይ ደስታህን ሙሉ የሚያደርግልህ ነገር ያለ አይመስለኝም። እስካሁንም ድረስ ውስጤ ያለ ነገር ነው። ሁልግዜም ይህን ነገር ወደ ኃላ ሳስብ ደስታ ይሰማኛል። ለምወደው ክለቤ በህይወቴ አንድ ነገር ሰርቻለው ብዬ አስባለው። ለዚህ ሁሉ ስኬት የቡድኑ ጥንካሬ፣ የእያንዳንዱ ልምድ ካለው ተጫዋች አንስቶ ከታች ካደጉት ተጫዋቾቹ ጨምሮ የነበራቸው አቅም፣ ህብረት ይህን ታሪክ የማይረሳውን ስኬት እንድናስመዘግብ አስችሎናል። በጊዜው በክለቡ በኩል የተደረገውን ስታስብ፣ በትልቁ ቢልቦርድ የቡድኑ ፎቶ በክበብ ውስጥ ተሰቅሎ ስታይ ምን ያህል ትልቅ ነገር እንደሆነ ታስባለህ። ባለፈው እንደ አጋጣሚ ወደ ኢትዮጵያ መጥቼ ሰዎችን ሰላም ለማለት ወደ መብራት ኃይል ክበብ ሄጄ ነበር። ገና ወደ ግቢው ስገባ በትልቁ የተሰቀለው ጊዜውን የሚያስታውስ ፖስተር ስመለከት ውስጤ የተሰማኝ ነገር ከፍተኛ ነበር። ምንም እንኳ ረጅም ጊዜ እንደመሰቀሉ ፖስተሩ በፀሀይ እና በዝናብ ፌድ ቢያደርግም። መልሰው ይቀይሩታል የሚል ነገር በጊዜው ሰምቼ ነበር። አሁን ያለውን ነገር አላውቅም ይቀይሩት አይቀይሩት። ሆኖም ግን ያንን ፎቶ ስመለከተው የተሰማኝ ስሜት ቀላል አልነበረም። የዘጠና ሦስት ድል ለእኔ ትልቅ ቦታ የምሰጠው፣ ሁሌም የማይረሳኝ ትልቁ ታሪኬ ነው”።በቀጣይ የፊታችን ዓርብ የዚህን የዘጠናዎቹ ድንቅ ተጫዋች አፈወርቅ ኪሮስን አጠቃላይ የእግርኳስ ህይወት የሚዳስስ ፁሑፍ ይዘን እንደምንቀርብ ከወዲሁ እንጠቁማለን።", "passage_id": "8fa1b415d391940327f0cafa56c5633e" }, { "passage": "በእግር ኳሱ መንደር የፍልሚያ ሜዳ ሲታይ ቁመቱ አጭር ግን ጠንካራ፣ መሮጥ የማይታክተው፤ ፈጣንና ጉልበታም ተጫዋች ነው። ተመልካች አድናቂዎቹም«እርሱ የምርጥነት ምልክት፤ አንድ ለሻምፒዮናነት የሚጫወት ክለብ ሊኖረው የሚገባውም ወሳኝ ተጫዋች ነው »ሲሉም ስለችሎታው ይመስክሩለታል። ሙሉ\nስሙ ኤዲን ሃዛርድ ይባላል። እኤአ 1991 የተወለደው ይህ ቤልጄየማዊ በጥበበኛ እግሩቹ ብቻም ሳይሆን በፀባዩም ይታወቃል። የዓለማችን እግር ኳስ ሶስተኛው ኮከብ ብለው የሚጠሩትም በርካታ ናቸው። አመለ ሸጋው ተጫዋች በእግር ኳሱ የፍልሚያ ሜዳ ከዳኛ ከተጫዋችና ደጋፊ ጋር በመነጫነጭና በእሰጣ አገባ ጊዜውን አያጠፋም። ትኩረቱ ሁሉ ኳሱና ኳሱ ላይ ብቻ ነው። ስራውን በሚገባ የሚያውቅ ታታሪ ሰራተኛ፤ በሽንፈትና በአቻ ውጤት ወቅት ደጋፊውን ከማክበሩ የተነሳ ቀና ብሎ ለማየት የማይደፍር ሽንፈት ውስጡ ድረስ ዘልቆ የሚሰማው መሆኑ ይነገርለታል። ከስነምግባሩ ባሻገር ስለድንቅ የአግር ኳስ\nጥበብ ክህሎቱ ተናግረው፣ የማይጠግቡም፤ የእርሱ በሜዳ ላይ መገኘት ብቻውን የአንድን ጨዋታ ውጤት ይወስናል፤ 90 ደቂቃ እርሱን ሜዳ ውስጥ መመልከት ብቻውን ደስታን ያጭራል ሲሉ ያሞካሹታል። በሁለት እግሩ ከሚጫወት ኤዲን ሃዛርድ ጋር የቡድን አጋሩ ከመሆን በተሻለ እርሱን በተቃራኒ መለያ መግጠም እጅግ አድካሚና ፈታኝ እንደሆነም ያምናሉ። በተክለሰውነት፣ በአካል ብቃትና በቴክኒክ ተሰጥኦ የታደለው ኤደን ሀዛርድ የእግር ኳስ ህይወት ይበልጥ ያማረና ወደ ከፍታው ማማ የተንደረደረው ከፈረንሳይ ነው። በተለይ በ2011/12 የውድድር ዓመት\nየፈረንሳይ ሊግ አንድ የሊል 20 ግቦችን በማስቆጠር16 ግቦችን ለቡድን አጋሮቹ ማቀበል የቻለ ሲሆን፤ የውድድር ዓመቱ ምርጥ ተጫዋችነት ክብርንም ተጎናጽፏል። ተጫዋቹ በፈረንሳይ ቆይታ በተለያዩ የአውሮፓ ሃያል ክለቦች አይን ውስጥ መግባት የቻለ ሲሆን ከሁሉ ቀድመው የግላቸው ማድረግ የቻሉት ግን ቼልሲዎች ናቸው። እኤአ በ2012 ሰማያዊዎቹን ሲቀላቀልም በወቅቱ ከለቡን የተቀላቀለበት የዝውውር ዋጋ\n32 ሚሊየን ፓውንድ ሆኖም ተምዝግቧል። ሃዛርድ የቼልሲዎችን ስብስብ ከተቀላቀለ ወዲህም በተለይ ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒዮም እኤአ በ2013 ስታንፎርድ ብሪጅ\nመድረሳቸውን ተከትሎ ይበልጥ ብቃቱን ማስመስከር ችሏል። ጆዜ ይከተሉት ለነበረው የ 4-2-3-1 የጨዋታ ፍልስፍና ይበልጥ ምቹ\nበመሆን የክለቡን የመልሶ ማጥቃት በማቀላጠፍ ስሙ ቀድሞ የሚነሳ ተጫዋች ለመሆን አልተቸገረም። በዚህ ብቃቱም ሰማያዊዎቹ በፕሪሚየር ሊጉ ዳግም እንዲያንሰራሩና በተከታታይ ድልና ወጥ በሆነ አቋም የሊጉን ዋንጫ እንዲያነሱ የእርሱ ተሳትፎና ሚና ከማንም ተጫዋች ገዝፎ ታይቷል። በቼልሲ ቤት ቆይታው ብዙዎች ስለ ችሎታው እንዲመሰክሩና ከመቀመጫቸው ተነስተው እንዲያጨበጭቡ ያስገደደው ሃዛርድ፤ በጣሊያናዊው አስልጣኝ አንቶኒዮ ኮንቴ እንዲሁም በማውሪዚዮ ሳሪ ጨዋታ ፍልስፍናም ከቋሚና ቀዳሚ ተመራጭ ተጫዋቾች እንጂ ተቀያሪ አልነበረም። በቼለሲዎች ቤት ላለፉት ሰባት ዓመታት የቆየው ሃዛርድ በየዓመቱ ድንቅ ብቃቱን እያስመሰከረና በብሪጅ ተመልካቾች ዘንድም ተወዳጅነቱን በማስጠበቅ የሰማያዊዎቹ ጥንካሬ ሚስጥር መሆን የቻለ ሲሆን፤ በተለይ ባሳልፍነው የውድድር ዓመት የ28 ዓመቱ\nቤልጄማዊ ጥበበኛ በማውሪዚዮ ሳሪ ስር 16 ግቦችን አስቆጥሮ 15 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ለቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ አቀብሏል፡፡ በምዕራብ ለንደኑ ክለብ የነገሰው ሃዛርድ በሚያሳየው ድንቅ ብቃት የፕሪሚየር ሊጉ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋችነት ክብርም ከመቋደስ ባለፈ፤ የባሎንዶር እንዲሁም የፊፋ ቤስት አዋርድ እጩ ውስጥ በተደጋጋሚ በእጩነት ስሙን አሰጥርቷል። ከዚህም ባለፈ ተጫዋቹን የግል ማድረግ የሚፈልጉ የዓለማችን ታላላቅ ክለባት ቁጥርም እንዲያይልም አድርጓል። በተለይ የስፔኑ ሃያል ክለብ ለተጫዋቹ የነበረው ፍቅር ከሁሉ ልቆ ታይቷል። ስሙ ከሎስ ብላንኮዎቹ ጋር የተዛመደው ሃዛርድ ከሰማያዊዎቹ ጋር የአንድ ዓመት ኮንትራት ቢቀረውም፤ በስታንፎርድ ብሪጅ ቆይታው ግን ከሚቀጥለው የውድድር ዓመት በኋላ እንደማይቀጥል በተደጋጋሚ ሲገለፅም ቆይቷል። ቼልሲዎቹ አርሰናልን በማሸነፍ የዘንድሮውን የአውሮፓ ሊግ ዋንጫ ባነሱበት ምሽት ሁለት ግቦችን ያስቆጠረው ሃዛርድ፤«የስንብቴ የመጨረሻ ቀን ይመስለኛል፤ በፕሪሚዬር ሊግ የመጫወት ህልም ነበረኝ፥ ላለፉት ሰባት ዓመታትም በአውሮፓ ታላቅ ከሆነው ቼልሲ ጋር ይህን አሳክቻለሁ፤ አሁን ሌላ አዲስ ፈተና በሌላ ሊግ ለመሞከር ተዘጋጅቻለሁ»ሲል ተደምጧል። ተጫዋቹ ከቼልሲ ለመልቀቅ ወስኖ ከሆነ ማረፊያው ሪያል ማድሪድ እንደሚሆን በተገመተው መሰረትም ባሳለፍነው ሳምንት ተጫዋቹ ሎስ ብናኮዎቹን በይፋ በመቀላቀል ሌላ ደማቅ ታሪክ ለመፃፍ ወደ ስፔን አቅንቷል። ከዊጋን ጋር የመጀመሪያ የሰማያዊ ማለያውን ጨዋታ ያደረገ ሲሆን፤ የመጨረሻ ጨዋታውም አርሰናል ሆኗል። የምእራብ ለንደኑ ክለብም የብዙዎች ዓይን ያረፈበትን እንቁ ልጃቸውን አሳልፈው ለመስጠትም ብዙ ቢማገቱም፤ በመጨረሻ ውድ ልጃቸውን አሳልፈው ለመስጠት ወስነዋል። በጥበበኛው ልጃቸው ምትክም 130 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ካዝናቸው አስገብተዋል። ተጫዋቹ በሳንቲያጎ በርናባው አምስት ዓመታትን ለመቆየት የሚያስችለውን ኮንትራት መፈረሙ ታውቋል። በሰባት ዓመታት የክለቡ ቆይታ በ352 ተጫታዎች ላይ\nተስልፎ የተጫወተ ሲሆን 110 ግቦችንም ከመረብ ማሳረፍ ችሏል። ሁለት የፕሪሚየር ሊግ፣ የአውሮፓ ሊግ፤ የኤፍ ኤና ሊግ ካፕ ዋንጫን ዋንጫን ከፍ አድርጎ መሳም ችሏል። ሃዛድ ይህን መሰል ታሪክ የሰራበትን ክለቡን መቀላቀሉን አስምልከቶም«አሁን ሪያል ማድሪድን መቀላቀሌ በይፋ ታውቋል፤ አንድ የማይካድ ነገር ቢኖር ደግሞ በእግር ኳስ ህይወቴ በወጣትነቴ የመጀመሪያዋን ግብ ካስቆጠርኩበት ጊዜ አንስቶ ለማድሪድ የመጫወት ህልም ነበርኝ»ሲል በማህበራዊ ድህረ ገፅ ላይ አስፈሯል። ቼልሲዎችን መሰናበት እጅጉን ከባድና ፈታኝ የውይወቱ ክስተቶች ሆኖቦት እንደነበርና ሆኖም ግን በአዲሱ ጎጆውም በብሪጅ የነበረው እያንዳንፈዱ ትዝታ አብሮት እንደሚጓዝ ሳይጠቁም አላለፈም። የቼልሲ ዳይሬክተር ማርያና ክራኖፋስኪያ፤ ከኤዲን ጋር መለያያት እጅግ አሳዛኝና ከባድ ነው። እኛ ከአርሱ ጋር ለመለያያት ፍላጎት አልነበረንም፤ ይሁንና ተጫዋቹ በሌላ አዲስ ፈተናና አዲስ አገር የልጅነት ራእዩን ለማሳካት የወሰነውን ውሳኔ እናካብራለን፤ በክለባችን ላበረከተው አስተዋፆኦም ምስጋናችን የላቀ ነው፤ ወደ ፊት ወደ ስታንፎድ ብሪጅ መመልስ ከፈለገም በራችን ሁሌም ለእርሱ ክፍት ነው ሲሉ»ተደምጠዋል። የቀድሞው የሪያል ማድሪድ ፕሬዚዳንት ሮማን ካልዴርኖም«ሃዛርድ በሁለት እግሩ መጫወት የሚችል ልዩ ተጫዋች ነው፤ በሜዳ ላይ ጥበብ እጅግ የተካነ ነው፤ ክለቡ ካስፈረማቸው ተጫዋቹች መካከልም ምርጡ ነው፤ በቀጣዩ ዓመት የአሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን ስብስብ ውስጥ ልዩነትን ማምጣት ይችላል»ብለዋል። በበርካቶች ዘንድ\nየሪያል ማድሪዶች ተስፋ\nመሆኑ የተሰመረበት ቤልጄማዊ\nጥበበኛ ዛሬም በይፋ\nየማድሪዶች ተጫዋች መሆኑን\nበማረጋጋጥ ከደጋፊዎቹ ጋር እንደሚተዋወቅ ይጠበቃል። የኳሱ\nጠቢቡ በአዲስ ቤት ለሌላ\nታሪክ ቀጣዩን የውድድር\nዓመት በናፍቆት ይጠብቃል።አዲስ ዘመን ሰኔ 4/2011 ታምራት ተስፋዬ", "passage_id": "9d7876a23ffd6a9a936c8000f43a3d71" }, { "passage": "ምሥሉ በዓለም ዙሪያ በትልልቅ አውደ ርዕዮች ቀርቦ አድናቆትን አትርፏል\n\n2ኛው የዓለም ጦርነት ማብቃቱን ተከትሎ አንድ የአሜሪካ ጦር መርከበኛ ድንገት በኒውዮርክ ጎዳና ላይ የነበረችን ቆንጆ ጎተት አድርጎ ከንፈሯን ጎረሰው። ምንም አላስተረፈም።\n\nያን ቅጽበት የፎቶ ጥበበኛው አልፍሬድ አይዠንስታድ በካሜራው አስቀረው። ያ ምሥል 'ላይፍ' በተባለው መጽሔትም ታተመ። ከዚያ ወዲህ በመጽሔቱ ብቻ ሳይሆን በሚሊዮኖች ልብ ላይ የታተመ የዓለማችን እጹብ ድንቅ ፎቶ ሆኖ ኖረ።\n\n• ባህልን በኤሌክትሮኒክ ሙዚቃ የቀመመው ሮፍናን\n\n• “ከወጡት ስራዎቼ ይልቅ ገና የሚወጡት ናቸው ትልቅ ቦታ ያላቸው” አለማየሁ ገላጋይ \n\n• ተፈጥሮን በብሩሽ የሚመዘግበው መዝገቡ\n\nያ ጎበዝ ሳሚ መርከበኛ ስሙ ጆርጅ ማንዶሳ ይባላል። በተወለደ በ95 ዓመቱ ትናንት ማረፉ ተሰምቷል።\n\nየ21 ዓመቷ ተሳሚ ቆንጆ ግሬታ ዚመር ፍሬድማን ትባላለች። በ2016 ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው። ኖራ ኖራ በ92 ዓመቷ ማለት ነው።\n\nየፎቶግራፍ ጥበበኛው አልፍሬድ አይዠንስታድ ያኔ ሳሚና ተሳሚዎቹ እነማን እንደሆኑ ሁሉ አልገለጸም ነበር። ኋላ ነው ነገሩ ይፋ የሆነው።\n\nእንደመታደል ኾኖ መርከበኛው የደንብ ልብሱን ለብሶ ድንገት እየበረረ አንዲትን ቆንጆ ሲስም ቅጽበቱን በካሜራ ቀለበው። ነገሩ ችሎታ ከምንለው ዕድል ብንለው ይቀላል። ይህ የሆነው ነሐሴ 14 ቀን 1945 ነበር።\n\n\"ድንገት በካሜራዬ ሌንስ ውስጥ አንድ ጉብል [ከሰልፍ መስመር ወጥቶ] ድንገት አንዲት ኮረዳን እንቅ አድርጎ ሲስማት ተመለከትኩ። የካሜራዬን ቁልፍ ተጫንኩት። ኮረዳዋ ነጣ ያለ የነርስ ደንብ ልብስ ነበር የለበሰችው። [ጎልታ ትታየኝ ነበር] እንዲያ ባትለብስ ኖሮ ይህን ምስል ስለማግኘቴ እጠራጠራለሁ\" ብሎ ነበር፤ አልፍሬድ።\n\n• ተፈራ ነጋሽ፡ \"በነገራችን ላይ ሙዚቃ አልተውኩም\"\n\nወይዘሪት ፍሬድማን ያኔ የጥርስ ሐኪም ረዳት ነበረች። ስለዚያ አስደናቂ ፎቶግራፍ ያወቀችው ግን ምስሉ ከወጣ ከ16 ዓመት በኋላ በ1960 ነበር።\n\n\"ያን ያህልም እኮ የፍቅር መሳሳም አልነበረም። እንዲሁ በፈንጠዚያ ላይ ነበርን፤ በቃ ይኸው ነው\" ብላ ነበር፤ ስለዚያ ፎቶግራፍ ስትናገር።\n\nዓለም ግን ይህን ፎቶግራፍ በዚያ መንገድ አልወሰደውም። ከብዙ እልቂት በኋላ ጃፓን ለአሜሪካ ጦር እጅ የሰጠችበትና የአሜሪካ አሸናፊነት የተበሰረበት ዕለትም በመሆኑ የዚያ ፎቶግራፍ ትርጉምና ዝና በአያሌው ገዝፎ ኖሯል።\n\n ", "passage_id": "de13deb7deb2fb6005f4671120e3a9cc" } ]
aaf8a6f85051d27a5fdaed808e41329c
5dda612370ba1f9820197ea13a3bf182
ኢትዮጵያ የፊፋን ጠቅላላ ጉባኤ ለማስተናገድ ዝግጅት ላይ ነች
የዓለምን እግር ኳስ የሚመራውና 211 አባላት ያሉት ፊፋ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ከአራት ወራት በኋላ ያደርጋል። ለአዘጋጅነቱ ደግሞ አፍሪካ የተመረጠች ሲሆን፤ የአህጉሪቱ መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባም ኃላፊነቱን ተረክባ ወደ ዝግጅቱ በመንደርደር ላይ ትገኛለች። ከሁለት ዓመታት በፊት የካፍን 60ኛ ዓመት ምስረታ ተከትሎ ጠቅላላ ጉባኤውን በስኬት ያጠናቀቀችው አዲስ አበባ ፤ 69ኛውን ጉባኤ ባሰናዳችውና ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖን ዳግም ለመሪነት በተመረጡበት የፓሪሱ ጉባኤ ላይ 70ኛውን መድረክ እንድታዘጋጅ መመረጧ ይታወቃል። ለዚህ የሚሆነውን ዝግጅት አስቀድማ የጀመረችው ኢትዮጵያ ለጉባኤው አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ከሰሞኑ ምክክር ያደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በድረ ገጹ አስነብቧል። ዝግጅቱን ለማድረግም ከስፖርት ኮሚሽን፣ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስትር፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት፣ የኢሚግሬሽን ጉዳዮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት፣ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ አየር መንገድ፣ ገቢዎችና ጉምሩክ፣ የወጣቶች ስፖርት አካዳሚ፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር፣ የብሮድካስት ባለስልጣን፣ ብሄራዊ መረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ የተውጣጡ አካላት ጥምረት ፈጥረዋል። ለጉባኤው ዝግጅት የሚያደርግ ብሄራዊ አብይ ኮሚቴም የተዋቀረ ሲሆን፤ የኮሚቴው የበላይ ጠባቂም የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ናቸው። ሰብሳቢዎቹ ደግሞ ኮሚሽነሩ አቶ ኤሊያስ ሽኩርና የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያሥ ጂራ መሆናቸው ታውቋል። በመጠናቀቅ ላይ ባለው ሳምንትም ኮሚቴው በዕቅድ ዝግጅቱ ላይ ውይይት ያደረገ ሲሆን፤ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጂሎ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያሥ ጂራ፣ የካፍ ተወካይ ወይዘሪት መስከረም ታደሰ እንዲሁም ሌሎች ተገኝተዋል። ጉባኤው ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የሚያስችል መነሻ ሰነድ ቀርቦም ምክክር ተደርጎበታል። በፊፋ ኮርፖሬት ኢቨንት ማናጀር ካትሪን አስተርበርገር በበኩላቸው ለጉባኤው ዝግጅት በቀዳሚነት መከናወን ያለባቸው ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። ከተማዋ ትልልቅ ስብሰባዎችን ለማስተናገድ አዲስ ባትሆንም ወሳኝ የሚባሉ ጉዳዮች ላይ ግን በተለየ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል። የመጀመሪያውም ከፊፋ አባላት ባሻገር ቁጥራቸው በዛ የሚል ሌሎች አካላትም በጉባኤው ወቅት የሚገኙ መሆኑን ነው ማናጀሯ የጠቆሙት። 1 ሺ400 ከሚሆኑት የጉባኤው ተሳታፊዎች ባሻገር 600 ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚና አፍሪካ ህብረት የሚሰሩ እንዲሁም ጉባኤውን ውጤታማ ለማድረግ የሚረዱ 300 ባለሙያዎች ከጉባኤው ሁለት ሳምንት አስቀድመው አዲስ አበባ የሚገኙ ይሆናል። በጉባኤው ተሳታፊ ለሚሆኑ አባል አገራት ተወካዮች ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት የትኛውን የቪዛ ዓይነት መጠቀም እንደሚገባቸው መለየት እንዲሁም የህክምና አገልግሎት በምን መልክ ማግኘት አለባቸው በሚል ቅድመ ዝግጅት ማድረግም ሌላኛው ነው። ጉባኤው ሲካሄድ በመንገዶች የትራፊክ መጨናነቅ እናዳይፈጠር፣ የመጓጓዣ አማራጮች እንዲሁም መጓጓዣዎች የአቅጣጫ አመልካች መሳሪያ መግጠም እንደሚያስፈልግም ማናጀሯ አሳስበዋል። ለጉባኤው አስፈላጊ የሆኑ መሳሪያዎች ወደ አገሪቷ ሲገቡ በገቢዎችና ጉምሩክ እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ትብብር እንዲያደርጉ፣ ጉባኤውን ለመዘገብ የሚገኙ የመገናኛ ብዙሃን የሚገቡበት ቪዛ ምን መሆን አለበትና የተሳታፊነት ማረጋገጫ ወረቀት በምን መልኩ ማግኘት አለባቸው በሚለው ጉዳይ ላይም ምላሽ መስጠት ይጠበቃል። ለቴሌኮም አገልግሎት የሚውሉ 400 ሲም ካርዶች፣ 4ጂ ኢንተርኔት እና የሬዲዮ መገናኛ ዘዴዎችን ማዘጋጀትም እንደሚያስፈልግና ለጉባኤው ተሳታፊዎች የደህንነት ዋስትና መስጠት እንደሚገባ ተጠቁሟል። አዲስ ዘመን ቅዳሜ ጥር 23/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=26501
[ { "passage": "ኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ 6ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን  አባላቶች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች፣ የደጋፊው ማህበር ተወካዮች እና የሚዲያ አካላት በተገኙበት በትናንትናው ዕለት በኔክሰስ ሆቴል አካሂዷል።ክለቡ በጉባዔው ያለፈውን ዓመት አፈፃፀም እና የ2009 ዓ.ም. የስራ ዕቅድ ከመገምገሙ በተጨማሪ የመተዳደሪያ ደንቡን ለማሻሻልም ውይይት አድርጓል።ተሳታፊዎች ወደስፍራው እስኪመጡ ድረስ የጉባዔው የመጀመሪያ ሰዓት የተራዘመ ሲሆን ከ39 የጠቅላላ ጉባዔው አባላት 25ቱ በመገኘታቸው ጉባዔው እንዲጀመር ሆኗል። የጠቅላላ ጉባዔው ሊቀመንበር አቶ ድንቁ ስለሺ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካሰሙ በኋላ መድረኩን ለክለቡ ቦርድ ፕሬዘዳንት መቶአለቃ ፈቃደ ማሞ ለቀዋል። መቶአለቃ ፈቃደ ማሞም የክለቡ ቦርድ አመራር አባላት የስራ ሪፖርትን ለጉባዔው አቅርበዋል።የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ስራ አስኪያጅ አቶ በላይ እርቁ የክለቡ የቴክኒክ፣ ፋይናንስ፣ የሰው ሃይል እና ጠቅላላ አገልግሎት እንዲሁም የገበያ አስተዳደር እና ማስታወቂያ ክፍሎች በ2008 ዓ.ም. የነበራቸውን የስራ አፈፃፀም ያቀረቡ ሲሆን እያንዳንዱ ክፍል የነበረውን ጠንካራ እና ደካማ ጎን ጠቅሰዋል።የቀድሞው የክለቡ አሠልጣኝ ድራጋን ፖፓዲች በነበራቸው ግልፍተኛ ባህሪ፣ ቡድንን የመምራት ችግር፣ ከቡድኑ ተጫዋቾች ጋር በነበራቸው አለመግባባት እና ከሌሎች የአሠልጣኝ ቡድኑ አባላት ጋር በምክክር መስራት ባለመቻላቸው ኮንትራታቸው እንዳይቀጥል መደረጉም በዚህ ወቅት ነበር የተገለፀው።አቶ በላይ እርቁ አያይዘውም የክለቡን የ2009 ዓ.ም. ዕቅድ ለጉባዔው ያሰሙ ሲሆን ዋናው የወንዶች ቡድን የፕሪምየር ሊግ እና ጥሎማለፉን እንዲያነሳ፣ የሴቶች ቡድኑ እስከ 5ኛ ደረጃ ድረስ ይዞ ሊጉን እንዲያጠናቅቅ፣ የተስፋ ቡድኑ ከ5 እስከ 7 ተጫዋቾችን ለዋናው ቡድን እንዲመግብ፣ እንዲሁም የ17 ዓመት በታች ቡድኑ በተመሳሳይ ከ5 እስከ 7 ልጆችን ለተስፋ ቡድኑ እንዲያበቃ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሆነ አስታውቀዋል። ከዚህ በተጨማሪ የቴክኒክ ክፍሉ አዲስ የተጫዋቾች ምልመላ መስፈርት መምሪያን እንዳዘጋጀ እና ይህንንም በአሁኑ ዓመት መጠቀም እንደሚጀምር ተነግሯል።በ2009 ዓ.ም. በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የክለብ የቴሌቪዥን ፕሮግራም መጀመር፣ በአቶ አህመድ ያሲን የተዘጋጀ ‘የእግርኳስ ረብሻ እና ነውጠኝነት ማስወገጃ ስትራቴጂ’ ለክለቡ ማህበረሰብ ማስተማር፣ አመታዊ ሩጫ ማዘጋጀት፣ የክለቡን መዝሙሮች ሲዲ እና ማልያዎችን ለገበያ ማቅረብ፣ ከነባር ስፖንሰሮች ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር እና አዳዲስ ስፖንሰሮችን ማምጣት የክለቡ የገበያ አስተዳደር እና ማስታወቂያ ክፍል በዕቅዱ የያዛቸው ነጥቦች ናቸው።ክለቡ በ2008 ዓ.ም. 32 ሚሊዮን ብር ገቢ የነበረው ሲሆን ከዚህ ውስጥ 28 ሚሊዮን ብሩን ወጪ አድርጓል። በያዝነው ዓመት ደግሞ 43 ሚሊዮን ብር አካባቢ የሚሆን ገንዘብ ለማስገባት እየተሰራ ሲሆን የክለቡ ጠቅላላ ወጪም ወደ 40.5 ሚሊዮን ብር እንደሚጠጋ ተገምቷል። የቡድኑን ውጤት ከፍ ለማድረግ ሲባል ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ ተደርጎ ተጫዋቾች መፈረማቸው፤ የአካል ብቃት፣ የሳይኮሎጂ እና የስነምግብ ባለሞያዎች ተቀጥረው ስራ መጀመራቸው እና የምግብ፣ የሆቴል፣ የትራንፖርት እና የመሳሰሉት አገልግሎቶች ዋጋ መናር ከአምናው ጋር ሲነፃፀር ወጪው የመጨመሩ ምክንያት ተደርገው ተቀምጠዋል።የክለቡ የ2008 ዓ.ም. የኦዲት ሪፖርት በኦዲት አማካሪው ድርጅት ተወካይ አቶ ኃብተወልድ መንክር ቀርቧል። በመጨረሻም ከ10 ዓመት በላይ በክለቡ አባልነት የቆዩ፣ ክለቡ የተለያየ ችግር ሲያጋጥመው በፋይናንስ እና በሌሎች መንገዶች የደገፉ፣ እንዲሁም በከፍተኛ አመራርነት አገልግለው የስራ ዘመናቸውን ሲጨርሱ ያላቸውን ልምድ ለአዲሱ አመራር እንዲያካፍሉ የሚፈለጉ ግለሰቦች በክብር አባልነት ተመዝግበው ድምፅ ሳይኖራቸው በጠቅላላ ጉባዔው ተሳትፎ እንዲያደርጉ የቀረበው ሃሳብ በስራ አመራር ቦርዱ ማሻሻያ ተደርጎበት በመተዳደሪያ ደንቡ እንዲካተት በመወሰን ጠቅላላ ጉባዔው ውሎውን አጠናቋል።", "passage_id": "1528afb74df6019e8dad8a122a9e34b6" }, { "passage": "በፕሬዝዳንቱ እና በሥራ አስፈፃሚዎች መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ዛሬ ሊካሄድ የነበረው የፌዴሬሽኑ ጠቅላላ ጉባዔ ወደ ሌላ ጊዜ ተላልፏል።በኢንተርኮንትኔታል ሆቴል ከጠዋቱ 03:00 ጀምሮ የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባዔ ለማድረግ ቀጠሮ መያዙ ይታወቃል። ሆኖም ምልዓተ ጉባዔው መሟላቱ ከተረጋገጠ በኃላ በፕሬዝዳንቱ አማካኝነት የመክፈቻ ንግግር ተደርጎ ም/ፕሬዝደንቱ አቶ በለጠ ዘውዴ የ2011 ሪፖርትም ሆነ የ2012 ዕቅድ እኛ የማናውቀው በፕሬዝዳንቱ ብቻ የቀረበ በመሆኑ አንቀበለውም በማለታቸው እንዲሁም አቶ ነጋሲ (የሥራ አስፈፃሚ አባል) ፌዴሬሽኑ የቡድን ሥራ አይሰራም፣ ህግ አይከበርም፣ ግለሰባዊ ነገሮች ይበዛሉ ይህ የሚቀርበው ሪፖርትም አናቀውም በማለታቸው በተጨማሪም የፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈለቀ ዋቄ የኦዲት ሪፖርቱ ማስታወቂያ ወጥቶ ውድድር ይደረግ ሲባል ከፅህፈት ቤቱ እውቅና ውጭ የተካሄደ በመሆኑ እና ሪፖርቱ እና እቅዱም በተመሳሳይ ከእውቅና ውጭ መፈፀም የለበትም በማለት ለጉባዔው አቅርበዋል።ፕሬዝደንቱ ኃይለየሱስ ፍስኃ በበኩላቸው ሁሉም ነገር የተካሄደው ህጉን ደንቡን መሠረት ያደረገ በመሆኑ የጠቅላላ ጉባዔው አባላት በ2011 ሪፖርት እና በ2012 ዕቅድ ዙርያ ሀሳብ ይስጥ በማለት መድረኩን ክፍት አድርገዋል።ከዚህ በኃላ የነበሩት የጉባኤው መንፈሶች እጅግ መግባባት የጎደለው በሥራ አስፈፃሚዎቹ በኩል የሰፋ ልዩነት የነበረበት እና መተማመን ያልሰፈነበት ሆኖ ቀጥሎ በመጨረሻም አሉ የተባሉ ችግሮችን አጣርተው ለቀጣይ ጠቅላላ ጉባዔ የሚያቀርቡ አምስት አጣሪ ኮሚቴ በድምፅ ብልጫ በመምረጥ ጉባዔው ወደ ሌላ ጊዜ ተላልፏል።የአጣሪ ኮሚቴ አባላትአቶ ዳንኤል ኃ/ሚካኤል\nአቶ ዐቢይ ካሣሁን\nአቶ ገዛኸኝ ታደሰ\nአቶ ሰለሞን\nአቶ ታምሩሌሎች ዝርዝር መረጃዎችን እንመልሰበታለን", "passage_id": "de16b50be7ecd706433444957ea9f45d" }, { "passage": "ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ አካል ፊፋ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በጻፈው ደብዳቤ የፕሬዚዳንትና የሥራ አስፈጻሚ አባላት ምርጫን የሚያስፈጽም አዲስ አስመራጭ ኮሚቴ እንደገና እንዲያዋቅር ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ፊፋ በፌዴሬሽኑ የፕሬዚዳንትና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫ ላይ የነበረውን ውዝግብ ለመፍታት ውሳኔ እንደሚያተላለፍ ከሳምንታት በፊት ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ፊፋ በደብዳቤው አዲሱ የአስመራጭ ኮሚቴ የፕሬዚዳንትና የሥራ አስፈጻሚ ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ልየታ እንደገና እንዲሠራና ወደ ምርጫ ሒደት እንዲገባም ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡በዚህም መሠረት የአስመራጭ ኮሚቴ አባላትን ለመምረጥ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ የሚጠራ ይሆናል፡፡", "passage_id": "19a303a83c3741849adc7012c267019e" }, { "passage": "የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2010 ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ ሲደረግ የፕሬዝዳንት ምርጫ እና የስራ አስፈፃሚ ማሟያ ምርጫውንም አከናውኗል።በኢትዮጵያ ሆቴል ከረፋዱ 4 ሰዓት ጀምሮ በተደረገው ጉባዔ የ2009 ቃለ ጉባኤን ማቅረብ እና ማፅደቅ፣ የ2010 የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ማቅረብ እና ማፅደቅ፣ የ2010 የኦዲት ሪፖርት ማቅረብ እና ማፅደቅ፣ የ2011 እቅድ ማቅረብ እና ማፅደቅ፣ ተሻሽሎ የቀረበውን የፌዴሬሽኑን ደንብ ማቅረብ እና ማፅደቅ እንዲሁም የፕሬዝዳንት እና የስራ አስፈፃሚ ሟሟያ ምርጫ ማካሄድ ተብለው በተቀመጡ አጀንዳዎች ላይ ውይይት ተደርጓል።ምልዓተ ጉባዔው በደንቡ መሰረት መሞላቱን በማረጋገጥ የተጀመረው ጉባዔው በእለቱ በተገኙት የክብር እንግዳ የመክፈቻ ንግግር ተጀምሯል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ኃይለሰማያት መርሃጥበብ ጉባዔው በይፋ መጀመሩን የማብሰሪያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በተለይ በአዲስ አበባ ስላለው ማዘውተሪያ ቦታዎች እጥረት ሃሳባቸውን አካፍለዋል። “እኔ ወደ ቦታው ስመጣ ገና ሁለት ሳምንት አልሞላኝም። ነገር ግን እኔ ወደ ቢሮው ከመጣው በኋላ በጥሩ መነሳሳት እየሰራን ነው። ከተማችን ውስጥ በርካታ ወጣቶች አሉ ነገር ግን እነዚህ ወጣቶች ስፖርት መስራት ቢፈልጉ እና እግር ኳስ መጫወት ቢያቹ ማዘውተሪያ ቦታ ስለሌለ ወደ አልባሌ ቦታ ይሄዳሉ። በስፖርቱ የአዲስ አበባ ችግር ደግሞ ይህ የማዘውተሪያ ቦታ ነው። ስፖርቱን በዜና በወሬ ብቻ ወጣቱ ከሚሰማው  ያለውን አቅም አውጥቶ እንዲጠቀም ከተማ መስተዳደራችን ከፍተኛ እቅዶችን አውጥቶ እየተንቀሳቀሰ ነው።” በማለት የነሱ ቢሮ በማዘውተሪያ ቦታዎች እና በፖሊሲዎች ዙርያ የፈለገው አካል ወደ እነሱ በመጠጋት ስራዎችን አብረው መስራት እንደሚችሉ ተናግረዋል።ከክብር እንግዳው ንግግር በኋላ የፌደሬሽኑ ጊዜያዊ ሰብሳቢ አቶ በለጠ ዘውዴ መድረኩን በመረከብ አጀንዳዎቹን ያስተዋወቁ ሲሆን ከተሳታፊ ተጨማሪ አጀንዳ ይያዝ የሚል ጥያቄ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል። በመጀመሪያ የ2010 የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በተለይ አምና እንደ እቅድ ተይዘው ሳይሰሩ የቀሩ ሃሳቦች ላይ ነጥቦች ተነስተዋል።በአፈፃፀም ሪፖርቱ ስለ ሲቲ ካፕ፣ ስለ ዲቪዚየኖች ውድድር፣ የማዘውተሪያ ቦታ፣ የቴክኒክ ጉዳዮች እና የመሳሰሉት ላይ ከጉባዔው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ተሰተው ውይይት ተደርጓበት መሻሻል አለባቸው በተባሉ ጉዳዮች ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ አደራ ተሰቶ በመተማመን እንዲፀድቅ ተደርጓል። ከአፈፃፀም ሪፖርቱ በመቀጠል የ2010 የኦዲት ሪፖርት በአቶ ሚካኤል አማካኝነት ቀርቦ ጉባዔው  ውይይት አድርጓበት በማፀደቅ ለምሳ ጉባዔው እንዲበተን ተደርጓል።ከምሳ መልስ በዋናነት የ2011 እቅድ እና የተሻሻለው የፌደሬሽኑ ደንብ ላይ የመከራከሪያ ነጥቦች ከተለያዩ ወገኖች ቀርበው ሃሳቦች ተንሸራሽረዋል። በተለይ ከአምስት አመታት በፊት ስራ ላይ የዋለውን የፌዴሬሽኑን ደንብ እንዲሻሻል በቀረበው አጀንዳ ዙሪያ ከጉባዔው በርካታ ሃሳቦች የተነሱ ሲሆን በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ እና ምላሽ እንዲሰጥባቸው ተደርጓል።በመቀጠል የፕሬዝዳንት እና የስራ አስፈፃሚ የሟሟያ ምርጫው የተከናወነ ሲሆን ድምፅ ከመሰጠቱ በፊት ምርጫውን በአስመራጭነት የሚመሩ ገለልተኛ አካላት ከጉባዔው የመምረጥ ድርጊት ተከናውኗል። ሶስት ገለልተኛ አስመራጮችን ከተመረጡ በኃላ ለፕሬዝዳንትነትም ለስራ አስፈፃሚነትም የሚወዳደሩ እጩ አካላት እራሳቸው እንዲያስተዋውቁ እና ስለሚሰሯቸው ስራዎች ማብራሪያ እንዲሰጡ ተደርጓል። ለፕሬዝዳንትነት ከሚወዳደሩት ሶስት እጩዎች አቶ አብዱልፈታ ተስፉ ባልታወቀ ምክንያት በቦታው ሳይገኙ በመቅረታቸው በቀጥታ ከውድድሩ ውጪ እንዲሆኑ እና በቦታው የተገኙት ሁለቱ ብቻ እንዲወዳደሩ የተደረገ ሲሆን ለስራ አስፈፃሚነት ከሚወዳደሩት 16 ግለሰቦች ኢ/ር የማታወርቅ አበበ እና አቶ ኤፍሬም ግዛው ባለተገለፀ ምክንያት እንዲሁም አቶ አስራት ሀይሌ እና አቶ ምትኩ መኩሪያ ከምርጫው ራሳቸውን በማግለላቸው ከእጩነት እንዲሰረዙ ተደርጓል።በዚህ ስነስርዓት ለፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩት እጩዎች በተፈቀደላቸው ሶስት ደቂቃ ሊሰሩ ስላሰቧቸው እቅዶች ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በተለይ ሁለቱም ግለሰቦች የውድድር ፎርማትን ስለማስተካከል እና በውድድር ላይ ተሳታፊ ስለሚሆኑ ክለቦች የአቅም ውስንነት ችግር መፍትሄ አለን በማለት ገለፃ አድርገዋል።በመቀጠል በቀጥታ ወደ ድምፅ አሰጣጥ ስነስርዓት የታለፈ ሲሆን ድምፅ መስጠት ከሚገባቸው 43 ድምፅ ሰጪዎች 35ቱ በመገኘታቸው ምርጫው እንዲከናወን ተደርጓል።በምርጫውም መሰረት ኢ/ር ሀይለየሱስ ፍስሃ በ20 ድምፅ አቶ ተስፋዬ ካሳይን በስምንት ድንፇች በመብለጥ አሸናፊ መሆናቸው እና አዲሱ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት መሆናቸው ተረጋግጧል። በስራ አስፈፃሚ የሟሟያ ምርጫው ድምፅ መሰረት ደግሞ አራት ግለሰቦች ተመርጠዋል። ወ/ሮ ሰርካለም ከበደ(18)፣ ዶ/ር አይናለም አባይነህ(17)፣ አቶ የኔነህ በቀለ(15)፣ አቶ ነጋሴ ሀለፉ(14) አዲሶቹ የስራ አስፈፃሚ አባላት መሆናቸው በድምፁ መሰረት ተረጋግጧል።ከምሳ ሰዓት በፊት በነበረው ውይይት ተጨማሪ አጀንዳ ይያዝ የሚል ሃሳብ ከጠቅላላ ጉባኤው በመነሳቱ ይህም ደግሞ የፌዴሬሽኑን ምክትል ፕሬዝዳንት ጠቅላላ ገባዔው ይምረጥ በተባለው መሰረት አዲሶቹ የስራ አስፈፃሚ እና ነባሮቹ የስራ አስፈፃሚዎች በምክትልነት መወዳደር እንደሚፈልጉ ጥያቄ ቀርቦላቸው ወደ ድምፅ አሰጣት ታልፏል። በዚህም መሰረት ምክትልነት እንፈልጋለን ብለው ከተወዳደሩት ዶ/ር ዘላለም፣ አቶ በለጠ እና አቶ የኔነህ አቶ በለጠ ዘውዴ በ24 ድምፅ በማሸነፋቸው የፌደሬሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።በስተመጨረሻ አዲሱ የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት ኢ/ር ኃይለየሱስ ፍስሃ ስለመረጡዋቸው ምስጋና አቅረበው ይህንን ብለዋል። “በመጀመሪያ አዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽንን በደንብ ይመራል ብላችሁ እና አምናችሁ ስለመረጣችሁኝ ከልብ ላመሰግናችሁ እወዳለው። ጥሩ እቅድ አቅርቤ እቅዴንም በአግባቡ ከምትጠብቁት በላይ ሰርቼ ላስደስታችሁ ስራዎችን እሰራለው” ብለዋል።", "passage_id": "9b561d0ae0d335c47f7cdf0ca8893f39" }, { "passage": "የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ዛሬ ህዳር 24/2012 ዓ.ም. ነው ሀላፊዎቹን በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ተቀብለው ያነጋገሩት፡፡\nውይይቱም ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ግንቦት በምታስተናግደው የአለም እግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ጉባኤ ላይ ያተኮረ ነበር የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት መረጃ እንደሚያመለክተው ፡፡\nኢትዮጵያ በቀጣዩ ግንቦት ወር የሚካሄደውን የዓለም እግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ጉባኤ ታስተናግዳለች።\nጉባኤው ዘንድሮ ለሰባኛ ጊዜ የሚካሄድ ነው፡፡\n", "passage_id": "b1f6db47de3275755e141db0752acbe1" } ]
83ccb37e190b1debf40524a3457f8cfe
a96f3084f819dc453f4d6cfcc8d681e9
እግር ኳስ የሞተበት ዕለት
ባለፉት ሁለትና ሦስት ዓመታት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ሜዳዎች ላይ ስርዓት አልበኝነት እየተንሰራፋ መምጣቱን ተከትሎ የ2012 ውድድር ዓመት ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ትልቅ ስጋት አንዣቦበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ እርግጥ ነው ባለፉት ዓመታት የታዩት የስቴድየም ሁከቶች አዝማሚያቸው አዲሱን የውድድር ዓመት ስጋት እንዲሰፍንበት ቢያደርግ አይገርምም፡፡ ይሁን እንጂ አስፈሪው ስጋት የበለጠ ጥፋት ሳያስከትል አልፎ አዲሱም የውድድር ዓመት በመልካም መንገድ ላይ ጉዞውን ቀጥሎ ፕሪሚየር ሊጉ ስምንተኛ ሳምንቱ ላይ ይገኛል፡፡ የስፖርታዊ ጨዋነት ጉዳይ ግን አልፏል ብለን የምንተወው ወይም ስጋት ሲፈጥርብን ብቻ የምናነሳው ጉዳይ አይደለም፡፡ ይልቁንም ካለፈው የምንማርበት ዘወትር የሌሎችን ተሞክሮና ታሪኮች አንስተን ነገን የተሻለ ለማድረግ የምንታትርበት መሆን ይገባዋል፡፡ በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችንም አንድ ሰው ለኩሶት የብዙዎችን ሕይወት የቀጠፈ ዓለማችን የማይረሳ የስቴድየም ግጭት መለስ ብለን በማስታወስ ከታሪኩ የምንማርበት እንዲሆን ወደድን፡፡ የዚህ ዘግናኝ የስቴድየም ግጭት ታሪክ ከዚህ ይጀምራል፡፡እኤአ ሰኔ 29 ቀን 1985፣ በሄይሰል ስታዲየም፣ ቤልጅየም የአውሮፓ የክለቦች ውድድር ፍፃሜ ነበር። የሊቨርፑልና ጁቬንቱስ ጨዋታ ሊጀመር ደቂቃዎች ቀርተዋል። በ1920ዎቹ በተገነባው ያረጀ ስታዲየም 58ሺህ ተመልካች ተጠቅጥቋል። የጁቬንቱስ ደጋፊዎች ከስታዲየሙ ‹‹Z›› ክፍል የላይኞቹ ደረጃዎች ወደ ታችኞቹ፣ አንዳቸው ሌላቸው ላይ ተነባብረው እየተገፋፉ ጎረፉ። የብረት ዘንግ የያዙ የሊቨርፑል ደጋፊዎች ያባርሯቸዋል። ተቀጣጣይ ነገሮች ይወረወሩባቸዋል። ሁከት ነገሠ። የራስን ነፍስ ለማዳን ሲባል በሌሎች ላይ መረማመድ ግድ ሆነ። መራወጡ፣ መደራረቡ፣ መተፋፈጉ ቀጠለ። ማዕበሉ ሄዶ፣ ሄዶ በስታዲየሙ ግድግዳዎች ተገደበ። የሰው ልጅ በማይቆጣጠረው ኃይል ተገፍቶ ከሸክላና ጡብ ከተሰራ አጥር ጋር ተጣበቀ። ግድግዳዎቹም ግፊቱን መቋቋም አቅቷቸው ፈረሱ። የስፖርት ቤተሰቡ ከአርማታ ስብርባሪ ጋር ተደባልቆ ተጨፈላለቀ። የ20 ዓመቱ ሲሞኔ ስተርን ወደ ጨዋታው የመጣው በአባቱ ጉትጎታ ነበር። የገዛው ቲኬት ጣዕረ ሞት በተንሰፈሰፈበት የስታዲየሙ ደቡባዊ ክፍል ‹‹Z›› ያስገባል። አንድ መግቢያ ብቻ ስለነበር በራፉ ላይ ትርምስ ተፈጥሯል። በቅጡ አልተፈተሸም፣ ደጋፊዎች ያለቲኬት በሩን ሲያልፉ፣ የቢራ ጠርሙስ የያዙም ሲገቡ ማየቱን ያስታውሳል። ወንበር የሌላቸው ደረጃዎች መቀመጫ ከሆኑበት ከዚህ የስታዲየሙ ክፍል የሊቨርፑል ደጋፊዎች ከተሰጣቸው ሌላው ክፍል ጋር ይጎራበታል። የሚለያቸው በኋላ የተደረመሰው የሽቦ አጥር ብቻ ነው። የመጀመሪያው ቁስ በአንድ ደጋፊ ገና እንደተወረወረ አባቱ ‹‹ከስታዲየም እንውጣ›› ብለው ሲሞኔን አጣደፉት። ጨዋታውን ሳይመለከት መውጣትን ባለመፈለጉ አባቱን ለመከተል አመነታ። በመዘግየታቸው ሁለቱም በሺዎች ተገፍተው ከግድግዳ ጋር ተጣበቁ። ነፍስ ግቢ፣ ነፍስ ውጪ ሆነባቸው። ሲሞኔ የሞት ሞቱን ግድግዳ ቧጦ፣ ሽቦ ተንጠላጥሎ በስታዲየሙ መፀዳጃ ቤት ጣሪያ ላይ ወጣ። ከዚያም አባቱን ከመታፈግና መረጋገጥ ለማዳን ከላይ ሆኖ ወደ ታች እጃቸውን ይዞ መጎተቱን ቀጠለ።‹‹አብሮን እንደነበረ የማናውቀው አንዳች ጉልበት በዚያች ሰዓት መጣልን። አባቴን ጎትቼ ወደ ጣሪያው አወጣሁት›› ይላል ሲሞኔ። ከመታፈጉ ሲወጡ ግን አባት እጃቸው ይደማ ነበር። የሞት ሞታቸውን ራሳቸውን አድነው በስታዲየሙ አጠገብ ወዳለ የቀይ መስቀል እርዳታ ማዕከል ሲሄዱ ተረጋግጠውና ተጨፈላልቀው የሞቱ ደጋፊዎችን አስከሬን መሃል ራሳቸውን አገኙ፡፡ ስርዓት አልበኝነት ባስከተለው ጣጣ 32 ጣልያናዊያን፣ አራት ቤልጅየማዊያን፣ ሁለት ፈረንሳዊያን እና አንድ ብሪታኒያዊ ህይታቸውን አጡ። የልጅ ልጆች ያሏቸው ኦቴሎ ሎረንቲን የ‹‹Z›› ታዳሚ ነበሩ። ከልጃቸው ሮቤርቶ እና ከሁለት የልጅ ልጆቻቸው አንድሪያ እና ግራኒ ጋር በዚሁ ቦታ የፍፃሜውን ጨዋታ ለመመልከት ወደ ሄይሰል መጥተዋል። ከእነርሱ ጋር የህክምና ባለሙያው ሮቤርቶ ሎረንቲን ነበር። በመገፋፋቱና በመረጋገጡ ሰዎች በመጎዳታቸው ሮቤርቶ የሙያውን ለማበርከት ጉዳተኞችን ሊታደግ ወደኋላ ቀረ ። ‹‹እንግሊዛዊያኑ የማይወረውሩብን ነገር የለም። ሮቤርቶ!… ሮቤርቶ!… ና ውጣ!… እንሂድ! ብዬ ተጣራሁ። ብረት፣ የአርማታ ፍንካችና ድንጋይ ወደኛ ይዘንባል። ህፃናትና ሴቶች አብረውን አሉ። እየተገፋን፣ እየተገፋን ከግድግዳው ጥግ ደረስን። ከዚያ ራሴን በቅፅበት በመጫወቻ ሜዳው ላይ አገኘሁት›› በማለት ኦቴሎ ክፉውን ቀን ያስታውሳሉ።‹‹ወደ ደረጃዎቹ እያየሁ ሮቤርቶን መጣራቴን ቀጠልኩ። በፍለጋዬ መሃል የእህቴ ልጅ አንድሪያ ጭንቅላቱን በሁለት እጁ ይዞ ከድንጋጤ ጋር ቆሞ አየሁት። የጠራሁት ሮቤርቶ በስታዲየሙ መቀመጫ ደረጃ ላይ ተንጋሏል። ጆሮዬን ከደረቱ ላይ አጣብቄ አዳመጥኩ። የሚሰማኝ የራሴው የልብ ትርታ ብቻ ነበር። ህይወቱ አልፏል። ይህን ሳደርግ የቴሌቪዥን ካሜራ ባለሙያ ይቀርፀኛል። በኋላም የሞተውን ልጄን ስፈልግ የሚያሳየውን ፊልም በቴሌቪዥን አየሁት።›› ይላሉ፡፡ሮቤርቶ ሌሎችን ለመርዳት ሲል ህይወቱን አጥቷል። የደጋፊዎች አስከሬን ተሰብስቦ በጊዜያዊ ማዕከል ተከማቸ። አባት ኦቴሎ ሌሊቱን የልጃቸውን አስከሬን ለመረከብ ወደ ሆስፒታል ሄዱ። ‹‹በሆስፒታል ከሶስት ሰዓታት በላይ አስጠበቁን። ሌሊት 9:00 ሰዓት ላይ የልጄን አስከሬን አየሁት። የአንገቱ ሃብልና የጋብቻው ቀለበት ተወስደዋል። ‹ማንነቱን ለመለየት ብለን ነው ያወለቅናቸው› የሚል ምክንያት ሰጡኝ። ነገር ግን በልጄ ጌጣጌጥ ላይ ስሙ አልተፃፈባቸውም ነበር። ሰርቀዋቸው ነው›› ይላሉ።የሞት ትራፊዎቹ ደጋፊዎች ስለሄይሰል ማውራት አይፈልጉም። ለብዙ ጁቬዎች የሄይሰል ስም ነውር ነው። ከአደጋው በኋላ አንድ ደጋፊ የመናገር አቅም አጥቶ ደንዝዞ ቃል ለመተንፈስ ወራት አስፈልገውታል። ሌላው ደጋፊ ደግሞ ከጓደኛው ጋር ወደ ስታዲየሙ መጥቶ በአደጋው ያጣውን ባልንጀራውን አስከሬን ከሙታኑ መሐል አገኘው። በሃዘን ወደ መኪናው ቢመለስም የመኪናው ቁልፍ እርሱ ዘንድ እንዳልሆነ አስታወሰ። በአስከሬኑ ኪስ ውስጥ ነበር። በወቅቱ የ14 ዓመት ታዳጊ የነበረ ደጋፊ የአባቱን መሞት ሳያውቅ በሰዎች ላይ በእግሩ ተረማምዶ ራሱን ማዳኑን ዛሬ በፀፀት ያስታውሳል። “ቢሆንም በባዶ እግሬ ነበርኩ። ጫማዬ በግርግሩ ከእግሬ ላይ ወልቆ ጠፍቶብኝ ነበር” እያለ ያዝናል። ከዚህ ሁሉ ትራጀዲ በኋላ ጨዋታው እንዲደረግ መወሰኑ አወዛጋቢ ነበር። በዚያ ርጉም ቀን ጨዋታው ቢቀጥልም ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የሊቨርፑሉ ማርክ ላውረንሰን የትከሻ ውልቃት ጉዳት ደርሶበት ተቀይሮ ወጣ። ጉዳቱ ከበድ ያለ ስለሆነ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ተወሰደ።“አምቡላንስ ውስጥ ተኝተህ ተጓዝ ተባልኩ። እኔ የፈለግኩት ደግሞ ተቀምጬ መሄድ ነበር። በድጋሚ እንድተኛ ታዘዝኩ። አሻፈረኝ አልኩኝ። እንደገና ኮስተር ባለ ትዕዛዝ እንድተኛ ተነገረኝ” ይላል። ትዕዛዙ የጠነከረበት፣ አንድ የሊቨርፑል ተጫዋች በአምቡላንስ ውስጥ መኖሩ እንዳይታወቅ ተብሎ ነበር። የመጣው ከእነ ማሊያው ነው። በላዩ ላይ የደረበበት የቱታ ጃኬትም ቀይ ነው። ማሊያውም ስለሚታይ ማንነቱን ለመለየት ቀላል ነበር። ሆስፒታል ሲደርስ በጓሮ በር አስገቡት። በሆስፒታሉ የሞቱትና ክፉኛ የቆሰሉት ደጋፊዎች ወገኖች ይገኛሉ። ሁሉም በሊቨርፑል ላይ አምርሯልና ላውረንሰን ተደብቆ መግባቱ ተገቢ ነበር። የወለቀ ትከሻውን በቦታው የመለሰው ቀዶ ጥገና ከተጠናቀቀ በኋላ ተጨዋቹን እዚያው አልጋ ላይ ተውት። አቅሉን መልሶ አግኝቶ ቀና ቢል አውቶማቲክ ጠብመንጃ የታጠቀ ወታደር በግርጌው ተቀምጦ አየ። ወታደሩም እጁን ዘርግቶ ፈጥኖ እንዲተኛ ምልክት ሰጠው። ላውረንሰንም ፈጥኖ ወደ አልጋው ተመለሰ።በነጋታው ጠዋት በባለቤቱና ከረዳት አሰልጣኞች በአንዱ ታጅቦ በድብቅ ከሆስፒታሉ ወጣ። የቤልጅየም ባለስልጣናትም አፋጥነው የሊቨርፑልን ተጨዋቾች ወደ ኤርፖርት ወስደዋቸው ወደ ሃገራቸው በረሩ። በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርጋሪት ታቸር ግፊት የእንግሊዝ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ክለቦቹ ከአውሮፓ ውድድሮች እንዲገለሉ አደረገ። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ደግሞ የሊቨርፑል ደጋፊዎችን ጥፋት ተመልክቶ የእንግሊዝን ክለቦች ለአምስት ዓመት ከማንኛውም ውድድር አገደ። ቅጣቱ ሄይሰል የተወውን የህሊና ጠባሳ ሊሽረው አልቻለም። በአንድ ደጋፊ የተጫረ ረብሻ ለብዙ ቤተሰቦች ጥልቅ ሐዘን ምክንያት ሆነ። ‹‹አዎን›› ይላል የወቅቱ የሊቨርፑል አምበል ፊል ኒል። ‹‹አዎን! በዚያ ቀን ምክንያት ከህይወት አስፈሪ ቅዠት ጋር ተጋፈጥኩ። ከጉዳቱ ለማገገምም ዘመናት አስፈለጉኝ።››አዲስ ዘመን ጥር 3/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=25533
[ { "passage": "ዲያጎ ማራዶናን\n\nበአገሩ የእግር ኳስ ንጉስ እየተባለ የሚንቆለጳጰሰው ማራዶና በ60 ዓመቱ ትናንት ረቡዕ ምሽት ሕይወቱ ማለፏን ተከትሎ በአርጀንቲና የሶስት ቀናት ሐዘን ተጀምሯል።\n\nየማራዶና አስክሬንም በመጪዎቹ ሶስት ቀናት የአርጀንቲና መንግሥት መቀመጫ በሆነቸው ካሳ ሮዛዳ እንደሚቆይ ተገልጿል።\n\nየማራዶና ሞትን ተከትሎ በርካቶች ሐዘናቸውንም እየገለጹ ይገኛሉ ነው። \n\n''ማራዶና እግጅ አስገራሚ ፍጥረት ነው፤ ነገር ግን እሱን መሆን በጣም ከባድ ነበር። ገና በለጋ እድሜው በታዋቂነቱ ምክንያት የመገናኛ ብዙሃን ትኩረትን ማግኘት ችሏል። እንደ ሌሎቻችን አይነት ሕይወት አላሳለፈም።'' ብሏል የማራዶና ቡድን አባል የነበረው ኦሲ አርዲለስ ከቢቢሲ ጋር ባደረገው ቆይታ።\n\nየቀድሞው የአርጀንቲና ኮከብ ተጫዋች እና በኋላም የአገሩ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበረው ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ያረፈው ቤቱ ውስጥ ሳለ በልብ ሕመም እንደሆነ ተገልጿል።\n\nማራዶና በዚህ ወር መጀመሪያ አካባቢ በአንጎሉ ውስጥ ላጋጠመው የደም መርጋት የተሳካ ቀዶ ሕክምና ተደርጎለት የነበረ ሲሆን በተከታይነትም ከአልኮል ሱስ ለመላቀቅ ሕክምና ይደረግለታል ተብሎ ነበር።\n\nትናንት ምሽት በተደረጉ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች መጀመሪያ ላይ ለማራዶና የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት የተደረገ ሲሆን በዚህ ሳምንት በሚደረጉ ሁሉም የአውሮፓ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ማራዶና ይታሰባል።\n\nሜሲ እና ሮናልዶን ጨምሮ ብራዚላዊው የእግር ኳስ ጥበበኛ ፔሌ እንዲሁም በርካታ የእግር ኳስ ፈርጦች በማራዶና ሕልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።\n\n''አንድ ቀን በሰማይ ቤት ከማራዶና ጋር እግር ኳስ እንደምንጫወት ተስፋ አደርጋለሁ'' ብሏል ፔሌ።\n\nየማንቸስተር ሲቲው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በበኩሉ ''የዓለምን እግር ኳስ ያሻሻል ሰው ነበር'' ብሏል።\n\nየቀድሞ የቶተንሀም አሰልጣኝና የአርጀንቲናዊው ማውሪሲዮ ፖቼቲኖ ''በሀዘን ልቤ ተሰብሯል። ማራዶና የእኔ ጀግና እና ጓደኛዬ ነበርክ። ከአንተ ጋር እግር ኳስና ሕይወትን በማየቴ በጣም ዕድለኛ ነኝ'' ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።\n\nየማራዶና ሕይወት\n\nየዓለማችን የምንጊዜም ታላላቅ ተጫዋቾች ከሚባሉት አንዱ የሆነው ማራዶና አርጀንቲና እአአ በ1986 የዓለም ዋንጫ ባለቤት ስትሆን የቡድኑ አምበል የነበረ ሲሆን ድንቅ ችሎታውንና የታወቀባቸውን የኳስ ጥበቡን በማሳየት ዓለምን አስደምሞ ነበር።\n\nበተለይ አርጀንቲና ከእንግሊዝ ጋር ባደረገችው የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ላይ እሱ \"የእግዜር እጅ\" ያላትና ዳኞች ሳያዩ በእጁ ያስቆጠራት ግብ ዘወትር ትታወሳለች።\n\nበተጨማሪም ለስፔኑ ባርሴሎናና ለጣሊያኑ ናፖሊ ቡድኖች በአውሮፓ ውስጥ የተጫወተ ሲሆን፤ በጣሊያን ሴሪ አ ውስጥም ሁለት ጊዜ ዋንጫ ማንሳት ችሏል። \n\nየአርጀንቲና እግር ኳስ ማኅበር የማራዶና ሞት በተሰማ ጊዜ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ባወጣው መግለጫ \"በጀግናችን ሞት በጣሙን አዝነናል\" በማለት \"ሁልጊዜም በልባችን ውስጥ ትኖራለህ\" ብሏል።\n\nማራዶና ለአገሩ አርጀንቲና በአራት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ በተደረጉ 91 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 34 ግቦችን አስቆጥሯል።\n\nማራዶና የተከለከሉ አበረታች መድኃኒቶችንና ዕጽ በመጠቀም ስሙ በተደጋጋሚ ሲነሳ የቆየ ሲሆን ከስፖርትም እገዳ ተጥሎበት ነበር።\n\nማራዶና ፕሮፌሽናል እግር ኳስን ከዛሬ 23 ዓመት በፊት በ37 ዓመት ዕድሜው ያቆመ ሲሆን፤ በአርጀንቲና ውስጥ ያሉ ቡድኖችን በአሰልጣኝነት ከመራ በኋላ የአገሩን ብሔራዊ ቡድንንም በማሰልጠን ለዓለም ዋንጫ አብቅቷል።\n\nከዚያም በኋላ በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ እና በሜክሲኮ ውስጥ የሚገኙ ቡድኖችን በተለያዩ ጊዜያት አሰልጥኖ ህይወቱ እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ደግሞ የአገሩን... ", "passage_id": "50c59aebb6c1af7e60d1562b5cb95e16" }, { "passage": " በአገራችን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በእግር ኳሱ ትልቅ ተፅዕኖ እያሳደሩ ከመጡ ክለቦች አንዱ ፋሲል ከነማ ስለመሆኑ ማረጋገጫ አያስፈልግም። ክለቡ የፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ መሆኑን ካረጋገጠ ወዲህ በጥቂት ዓመታት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልታና ማገር የሆኑ በርካታ ተጫዋቾችን ከማበርከት ባለፈ በፕሪሚየር ሊጉ የዋንጫ ተፎካካሪ በመሆን በተደጋጋሚ ዓመታት ጥንካሬውን አሳይቷል። በቁጥርም በውበትም የእግር ኳሱን ቤተሰቦች ያስደመሙ ደጋፊዎችን በማበርከትም ካምቦሎጆን ካደመቁ ጥቂት ክለቦች መካከል አንዱ ሆኗል። የውብ ደጋፊዎች ባለቤት የሆነውን ፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ከብዙ በጥቂቱ በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችን እንደሚከተለው ለመመልከት ወደድን።1960 ዓ.ም ጎንደር ከተማ ላይ የያኔ ወጣቶች በአገሪቱ የነበሩ ትልልቆቹን የእግር ኳስ ቡድኖች (አሥመራ ቡድን፣ ሸዋ ቡድን፣ አየር ኃይል ቡድን፣…) እያሰቡ፤ አንድ ትንሽ የእግር ኳስ ቡድን በራሳቸው ጥረት መሰረቱ። በጨርቅ ኳስ የተጀመረው የእግር ኳስ ቡድን ስብስብ ብዙ የተለየ እንቅስቃሴ ሳያድርግ ስድስት ዓመታት ተቆጠሩ። ስብስቡ የሰፈር ጨዋታዎችን ከማካሄድ ሳይሻገር ኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ አስተናገደች። ሕዝባዊ አብዮት። የ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት የአገሪቱን ፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ መዋቅሮች ብቻከገጽ 20 የዞረሳይሆን ማህበራዊ መዋቅሩንም ቀየረው። የለውጡ አካል የነበረችው ጎንደር፤ በሥር ነቀል ሂደቱ ውስጥ ስታልፍ በከተማው ውስጥ ከስድስት ዓመታት በፊት የተመሰረተው የእግር ኳስ ቡድን እንደዘመኑ መንፈስ አዲስ የቡድን ስያሜ ያዘ። ‹‹ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን›› ተሰኘ። አሁን ጊዜው 1967 ዓ.ም ሆኗል።የትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾች በአብዛኛው የቀበሌ 16 በተለምዶ ‹‹ቸቸላ›› ተብሎ የሚጠራው ሰፈር ልጆች ናቸው። በጊዜ ሂደት ግን ከየአቅጣጫው ቡድኑን የተቀላቀሉት የከተማዋ ወጣቶች አልጠፉም። መካሻ፣ አባቡ፣ ሰጠኝ፣ አራጋው፣ … የትግል ፍሬ እግር ኳስ ቡድን ሞተር ነበሩ። በእግር ኳስ ያበደ ልባቸው በፖለቲካ ለመቅለጥ ጊዜ አልፈጀበትም። አብዛኛዎቹ የቡድኑ አባላት በኢህአፓ የፖለቲካ መስመር ተጠለፉ። እንደዘመኑ መንፈስ፤ ህብዑ ገቡ። ይህም ሆኖ ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ከአቻዎቹ ጋር የእግር ኳስ ግጥሚያ ከማካሄድ አልቆመም። የግጥሚያ ሜዳው በየጊዜው ይቀያየር ነበር። ጎንደር ሆስፒታል ግቢ ውስጥ በተለምዶ ‹‹ኳስ ሜዳ›› ተብሎ በሚጠራው ሜዳ፣ ፋሲለደስ መዋኛ ግቢ ፊት ለፊት (ዛሬ ላይ ፋሲለደስ ስታዲየም ተብሎ የተሰየመው)፣ ፋሲለደስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ፣ … የእግር ኳስ ውድድሮች በተዘጋጁ ቁጥር ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ተሳታፊ ነበር።የደርግ ምህረት የለሽ ቅጣት በኢህአፓ ወጣቶች ላይ እየበረታ ሲመጣ፣ የመላኩ ተፈራ ፈርዖናዊ እብሪት በጎንደር አደባባዮች ላይ ናኘ። ከተማዋ በደም አበላ ታጠበች። ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ቅርቃር ውስጥ ገባ። የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋቾች መመናመን ጀመሩ። ያም ሆኖ የቀይ ሽብር ዘመን አልፎ እንኳ ቡድኑ አልከሰመም። መደብዘዙ ግን አልቀረም።ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ‹‹ዓለም የለምም›› ሳይባል ዓመታት ነጐዱ። ደርግ በድራማዊ አጀብ እንደተከሰተው፤ በትራጄዲ ሁነት ተሰናበተ። ትግል ፍሬ እንደ አጀማመሩ ባይሆንም ቡድኑ በሥም ደረጃ ይንቀሳቀስ ነበር። ከደርግ ውድቀት በኋላ ግን ትግል ፍሬ በስምም ከሰመ። ለሁለት ዓመት ብቻ። 1985 ዓ.ም የትግል ፍሬ ተከታይ ትውልድ በአዲስ መንፈስ ‹‹ፋሲል›› በሚል ሥያሜ የእግር ኳስ ቡድን ተቋቋመ። ፋሲል ከነማ የሚለው ስያሜ የሽግግር መንግሥቱ ጊዜ ካበቃ በኋላ በተፈጠረው የከተሞች አደረጃጀት የመጣ ስያሜ መሆኑ እዚህ ላይ ይነሳል።1985 እና ከዛ በኋላ የነበሩ ዓመታት እንደ ቀዳሚዎች ዓመታት ከፖለቲካና ኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች አኳያ ለጐንደር ፈታኝ ጊዜያት ነበሩ። ማህበራዊ ቀውሶች በተጨማሪነት ቢስተዋሉም በእግር ኳስ ረገድ ግን ጥሩ መነቃቃት ነበር። ዛሬ ላይ ‹‹ታየ በላይ ሆቴል›› የተገነባበት ቦታ ‹‹ሜክሲኮ ሜዳ›› ይባል ነበር። በዚህ መለስተኛ ሜዳ በመሬት አርድ የእግር ኳስ ደጋፊዎች የታጀበ የእግር ኳስ ውድድር መርሃ ግብሮች ይካሄዱ ነበር። አራዳ፣ ውሃ ልማት፣ ፖሊ፣ ኳሊበር፣ ኒያላ፣ ኢዲዲሲ … የተሰኙ የእግር ኳስ ቡድኖች ቀንደኛ ተፋላሚዎች ነበሩ። ከእነዚህ ቡድኖች ውስጥ የተሻለ የመጫወት ጥበብ ያላቸው ተጫዋቾች ለፋሲል እግር ኳስ ቡድን መጋቢ በመሆን አገልግለዋል። የያኔው ፋሲል ከ‹‹ሜክሲኮ›› ጨዋታ ከፍ ባለ መልኩ ከወረዳ የእግር ኳስ ቡድኖች ጋር ይጫወት ነበር። ‹‹ፋሲል ከነማ የትውልዶች ቅብብል ውጤት ነው›› የሚባለውም ለዚህ ነው።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አደረጃጀትና የአሰራር ዝግመታዊ ለውጥን ተከትሎ ፋሲል ከነማ ለዓመታት በከተማ ደረጃና በብሔራዊ ሊግ ደረጃ ሲጫወት ቆይቶ፤ በ2008 የውድድር ዘመን ብሄራዊ ሊጉን በበላይነት በማጠናቀቅ የኢትዮጵያ ፕሪሚሪ ሊግ ተሳታፊ ለመሆን በቃ። የትውልድ ቅብብሎሽ በታየበት በዚህ የታሪክ ሂደት መሰረት ክለቡ 50 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ አንጋፋ ክለብ ነው።‹‹ፋሲል ከነማ በትውልዶች ቅብብል የቆመ የከተማችን እግር ኳስ ክለብ ነው›› የሚለው አቋም የክለቡ ደጋፊዎች የጋራ ምልከታ ነው። በተለይም ክለቡ በብሔራዊ ሊግ ቆይታው በነበረበት የገንዘብ እጥረት የተነሳ ፈታኝ ጊዜያትን አሳልፏል። በ2008 ዓ.ም የብሔራዊ ሊጉ የውድድር ዘመን ፋሲል ምድቡን በበላይነት እየመራ እንኳን ከተማ አስተዳደሩ ለክለቡ የበጀተው በጀት በዓመቱ አጋማሽ አልቆ ነበር። በክለቡ ስም የንግድ ትርዒት (ባዛር) እና የሙዚቃ ዝግጅት (ኮንሰርት) በማዘጋጀት ገቢ በማሰባሰብ፤ በጐንደር ዩኒቨርሲቲ ድጋፍ፤ በከተማው ወጣቶችና አጋር የስፖርቱ ቤተሰቦች ጥረት እንዲሁም ዳሽን ቢራ ፋብሪካ በሰጠው ገንዘብ ዓመቱን እንደምንም ቆይቶ ብሔራዊ ሊጉን በድል በማጠናቀቅ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ለመቀላቀል በቃ።ለብዙዎቹ የአገሪቱ እግር ኳስ ተከታታዮች ክስተት በሆነ መልኩ የፋሲል ከነማ ስኬታማ የሚባል ጉዞ ያለ ደጋፊው ማዕበል የሚታሰብ አልነበረም። የክለቡ ደጋፊዎች ፋሲል ከነማን እንደ አንድ የጎንደር የታሪክ አካል አድርገው ይመለከቱታል። ከዚህ ምልከታቸው በመነሳት ለክለቡ የሚያደርጉትን ድጋፍ ማቀጣጠያ ዘዴያቸውም ታሪክ ነው። ‹‹የጎንደር ክብሯ ታሪኳ ነው›› የሚሉት የክለቡ ደጋፊዎች፤ የፋሲል ከነማ ክለብ ዋና መለያ ‹‹አፄዎቹ›› ሆኗል። በፖለቲካ አፈና፣ በማህበራዊ ሕይወት ብክነትና በኢኮኖሚ መገፋት ተበታትነው የነበሩት የጎንደር ከተማና አካባቢዋ ወጣቶች ፋሲል ከነማ ምክንያት ሆኗቸው በአንድነት ጥላ ስር ተገናኝተዋል። በፋሲለደስ ስታዲየም፤ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱና ጓዶቹ ስማቸው እየተነሳ ተዘምሮላቸዋል። አርበኛ ጐቤ መልኬ ታስቦበታል። ዛሬ ላይ ፋሲል ከነማ በአገሪቱ ቀዳሚ የደጋፊ ሃብታም ከሚባሉ ክለቦች አንዱ ብቻ ሳይሆን ጠንካራ ተፎካካሪም ሆኗል። የድጋፍ መሰረቱ የሰፋውን ያህል ግን የገቢ አቅሙን ማሳደግ አልቻለም። ትላንት፣ ዛሬም ሆነ ነገ ዘመናዊ አደረጃጀትና ዘላቂ የገቢ/ስፖንሰር ምንጭ ዕጥረት የክለቡ ፈተና ሆነው ይቀጥላሉ። ፋሲል ከነማ ካስቆጠረው ዕድሜና ከመጣበት የታሪክ ሂደት አኳያ በአደረጃጀት ተገቢ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል ማለት ስህተት ይሆናል። በየዘመኑ ግን ህያው የሕዝብ ድምፅ በመሆን የትውልድ ቅብብሎሽ አርማ ሆኖ አገልግሏል። እያገለገለም ነው።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 11 ቀን 2012 ዓ.ም ቦጋለ አበበ", "passage_id": "c2116d9c852f65fce77b7b7a9de24ef3" }, { "passage": " ብራዚል ለአንድ ወር ያህል ያስተናገደችው ሃያኛው የዓለም ዋንጫ ዛሬ ፍፃሜ ላይ ይደርሣል፡፡ለዋንጫው አርጀንቲናና ጀርመን እየተፋለሙ ነው፡፡አዲስ አበባ ላይ ሁኔታው ምን ይመስላል፡፡ጨዋታው ከመጀመሩ ከአንድ ሰዓት በፊት እስክንድር ፍሬው ያደረገውን ቃለ-ምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡ እስክንድር ጀርመን ይላል - እርስዎስ? ", "passage_id": "b97db93044a42959ba9da8481ddd4382" }, { "passage": "ትግራይ ስታዲየም\n\nበ2009 ዓ.ም በርካታ ቁጥር ያለው የስቴዲየም ብጥብጥ በተለይም በላይኛው ፕሪሚየር ሊግ ቢዘገብም ከብጥብጦቹ ጀርባ እግር ኳስን የሚሻገሩ ገፊ ምክንያቶች እምብዛም እንዳልነበሩ ይጠቀሳል።\n\nበያዝነው ዓመት በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚለኮሱ ግጭቶች እና ረብሻዎች ቁጥር አይሏል። \n\nከተጀመረ ጥቂት ሳምንታትን ብቻ ባስቆጠረው የ2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ከረብሻዎች ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በተለያዩ ክለቦች ላይ የጣለው ቅጣት ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደደረሰ ጉዳዩን የሚከታተሉ ባለሞያዎች ያስረዳሉ።\n\nመጠናቸው ይለያይ እንጅ ባለፉት ሁለት ወራት ሃዋሳ፣ ድሬዳዋ፣ አዲግራት፣ ጅማ እና በቅርቡ ደግሞ ወልዲያ ከተሞች ውስጥ ግጭቶች እና ረብሻዎችን አስተናግደዋል።\n\nባለፈው እሁድ በወልዲያ ስፖርት ክለብ እና በመቀሌ ከተማ መካከል ሊደረግ የነበረው የእግር ኳስ ጨዋታ ከመጀመሩ ከሰዓታት በፊት በሁለቱ ቡድኖች ደጋፊዎች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ህይወት የጠፋ ሲሆን ንብረት ላይ ዘረፋና ወድመት ተከስቷል።\n\nበዕለቱ ማገባደጃ ላይ በመቀሌ ከተማ መንገዶች ላይም ክስተቱን ለመቃወም በርካታ ሰዎች ወጥተው ነበር። ጨዋታው ካለመካሄዱ በተጨማሪ የግጭቱ አሻራ እስከቀጣይ ቀናት ቀጥሏል። \n\nየትግራይ ክልል የእግር ኳስ ፈዴሬሽንም ክስተቱን በማውገዝ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈደሬሽን ጉዳዩን ኣጣርቶ በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዲወስድ በደብዳቤ ጠይቋል።\n\nየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ባሻ የወልዲያው ክስተት ከእግር ኳስ የሚሻገር ገፅታ እንዳለው ይገልፃሉ።\n\nበሴካፋ ውድድር ከሚሳተፈው የወንድ አዋቂዎች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ጋር ናይሮቢ የሚገኙት አቶ ጁነዲን ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ግጭቱ ከስፖርት ሜዳ ውጭ መቀስቀሱን አስታውሰው \"ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ይዘት ያለው ነገር ነው። ሜዳ ውስጥ ቢሆን ከኳስ ድጋፍ ጋር ይያያዝ ነበር፤ ሌላ ትኩሳት ያለበት ነው የሚመስለኝ፤ እግር ኳስ ብቻውን አይመስለኝም\" ሲሉ ተናግረዋል።\n\nከማኅበረሰባዊነት እስከ ብሔረተኛነት\n\nበስፖርቱ ዓለም የተመልካቾች ነውጠኛነት ምክንያቶች ብዙ ናቸው ሲል የሚያስረዳው የስፖርት ተንታኙ መንሱር አብዱልቀኒ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ ወይንም ምጣኔ ኃብታዊ ብሶቶች ስቴዲየም ላይ ሊያጠሉ እንደሚችሉ ይናገራል። \n\nበኢትዮጵያ እግር ኳስን የታከከ ብጥብጥ ሲከሰት \"የመጀመሪያው ባይሆንም እየተባባሰ ግን ሄዷል። የቅርብ ጊዜ ክስተቶችን ስናጤን ደግሞ ከእግር ኳስ ባሻገር ሌሎች የጀርባ ምክንያቶች እንዳሉ ግልፅ ነው\"ይላል።\n\nእግር ኳስ ማኅበረሰባዊ መሰረት ከሌለው በስተቀር የጠነከረ የእኔነት ስሜት ሊፈጥር አይቻለውም የሚለው መንሱር፤ ይሁንና ክለቦች ከማኅበረሰባዊ መሰረታቸው በዘለለ ብሔር ተኮር መልክን እየተላበሱ የመምጣታቸውን አዝማሚያ \"አደገኛ ነው\" ይለዋል።\n\n\"ከአንዳንድ በጥባጭነት እጅግ ወደተደራጀ ነውጠኛነት ሊሄድ ይችላል። ቀስ በቀስ ወደመቧደን እየተሄደ ነው። ራሳችንን መከላከል እና ማዘጋጀት አለብን በሚል ደጋፊዎች ራሳቸውን ማደራጀት ከጀመሩ የሚያሰጋ ዓይነት እውነታ ሊፈጠር ይችላል።\"\n\nላለፉት ሁለት ዓመታት መቀሌ ከተማ የእግር ኳስ ክለብን የደገፈውና ባለፈው እሁድ ማለዳ የወልዲያ አመሻሹን ደግሞ የመቀሌ ኹከቶችን የታዘበው ገብረመድህን ኃይለስላሴ በዚህ አስተያየት ይስማማል።\n\n\"የእኔነቱ መንፈስ ከርሮ ከኳስ ወዳጅነት ወደብሔርተኝነት ነው እየሄደ ያለው፤ ከዚህ ቀደም ብጥብጡ ተጀምሮ የሚያልቀው ስቴዲየም ነው፤ ከዚያ አያልፍም። አሁን አሁን እየታየ ያለው ግን የባሰ ነው\" ሲል ለቢቢሲ አስተያየቱን ሰጥቷል።\n\nየፋሲል ከነማ የእግር ኳስ ክለብን የሚደግፈውና የድጋፍ እንቅስቃሴዎችን... ", "passage_id": "6439fb0061a049795c4a01718f0e6d35" }, { "passage": "  በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። የወቅቱ የዓለም ራስ ምታት በሆነው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር በተያያዘም ስፖርት መገኘት ባለበት ሁሉ አጋርነቱን በማስመስከር ላይ ይገኛል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮችን ከማቋረጥና ከመሰረዝ ባለፈ የስፖርቱ ተዋንያን በተናጥልም ሆነ በተቋማዊ ደረጃ አበርክቷቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በእግር ኳስ ጠቢብነታቸው ዓለም የመሰከረላቸው ተጫዋቾችና ስመ ጥር አሰልጣኞችም፤ ለደጋፊዎቻቸው መልእክት ከማስተላለፍና ገንዘብ ከመለገስ ባሻገር ሆቴሎቻቸውን ለህክምና አገልግሎት እንዲውሉም ጭምር መስጠታቸው ይታወሳል። ክለቦችም በተመሳሳይ ስታዲየሞቻቸውን ቫይረሱን ለመዋጋት ለሚደረገው ጥረት እያዋሉት ይገኛሉ። የነጫጮቹ ስታዲየም ሳንቲያጎ በርናባው ለቫይረሱ የሚሆኑ መድሃኒቶችና የህክምና እቃዎች ማከማቻ በመሆን እያገለገለ ይገኛል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ተከትሎ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እየደረሰ እንደሚገኝ ይታወቃል። ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያንቀሳቅሱ ዘርፎች መካከል አንዱ የሆነው ስፖርትም በዚሁ ምክንያት የገንዘብ ችግር በማስተናገድ ላይ ይገኛል። ከዚህ ጋር በተያያዘም የፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች ለተጫዋቾቻቸው ሙሉ ደሞዛቸውን መክፈል ከማይችሉበት ደረጃ ደርሰዋል። ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በጊዜያዊነት እስከ መጪው ወር መጨረሻ ድረስ መቋረጡ ይታወሳል። ክለቦች ከስታዲየም ገቢ እና ለሌሎችም የሚያገኙት ገቢ ላይ መቀነስ ተከትሎ ከፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ተጫዋቾቹ የደመወዛቸው ግማሽ እንዲከፈላቸው በመስማማት ስፖርት የመተሳሰብ መድረክ መሆኑን አረጋግጠዋል። ጥያቄውን በቅድሚያ ያቀረበው የሊጉ ክለብ የሆነው በርሚንግሃም ሲቲ ሲሆን፤ ለአራት ወራት በዚህ መልክ ደመወዝ እንደሚከፍል ማስታወቁን ዘጋርዲያን በዘገባው አስነብቧል። ቅድሚያ አንዳንድ ተጫዋቾች ሃሳቡን ባይቀበሉም በሂደት በበጎ ፈቃደኝነት መስማማታቸውን አሳይተዋል። ክፍያው ከተጫዋቾችና የአሰልጣኞች ቡድን ባለፈ ያሉ የክለብ ሰራቶችን እንደማይመለከትም ታውቋል። ወደ ኢትዮጵያ መለስ ስንልም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 2 ሚሊዮን ብር ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል እንዲሁም ለታላቁ የህዳሴ ግድብ መስጠቱ ከትናንት በስቲያ የተሰማ ዜና ነው። ይህም ብቻ ሳይሆን የፌዴሬሽኑ ተቀዳሚ ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉም በግሏ ለጤና ሚኒስቴር እንዲሁም ለታላቁ የህዳሴ ግድብ በድምሩ 400ሺ ብር መለገሷ ታውቋል። የኢትዮጵያ ዳኞችና ታዛቢዎች ሙያ ማህበርም በበኩሉ ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የ 50ሺ ብር ድጋፍ አድርገዋል። የወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ምክትል ፕሬዚዳንት የገንዘብ እንዲሁም የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ለመጓጓዣ እንዲውል የተሽከርካሪ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ሶከር ኢትዮጵያ በድረ ገጹ አስነብቧል። ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "7d1c97ca5be7fde3506bae56ae7df06b" } ]
2ffab085bcde96878ab471f77c129a1b
4abdda6159a37f75babcfa93a4eb706b
አትሌቶች የፖለቲካ መልዕክት እንዳያስተላለፉ የተሰጠው አወዛጋቢ ማሳሰቢያ
በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አትሌቶች የትኛውንም ዓይነት የፖለቲካ፣ የሃይማኖት፣ የዘርና መሰል ተቃውሞና መልዕክት እንዳያስተላልፉ የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ አሳሰቡ። ፕሬዚዳንቱ የ2020 የፈረንጆች አዲስ ዓመትን በተመለከተ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት ‹‹የኦሊምፒክ መድረክ በፍፁም የፖለቲካ ተቃውሞ፣የሃይማኖትና የዘረኝነት መልዕክት የሚተላለፍባቸው መሆን የለበትም›› ብለዋል። በኦሊምፒኩ ወቅት በየትኛውም ስፍራ አትሌቶች ለተፎካካሪዎቻቸው ክብር ማሳየት እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። ቶማስ ባኽ ስፖርትን የፖለቲካ መጠቀሚያ የማድረግ አዝማሚያ እየሰፋ በመጣበት በዚህ ወቅት በኦሊምፒክ መድረክ አላስፈላጊ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ምንም ጥቅም እንደሌለውና የዓለምን ሕዝቦች ከመነጣጠል የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው አብራርተዋል። ‹‹የኦሊምፒክ መድረክ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው አትሌቶች ስፖርታዊ ብቃታቸውን የሚያሳዩበት እንጂ የፖለቲካ ወይም ሌላ ፕሮፓጋንዳ የሚያስተላልፉበት አይደለም›› ያሉት ቶማስ ባኽ ስፖርትን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለመታገል በመድረኩ እንደዚህ ዓይነት ማሳሰቢያዎችን ቀድሞ ማሳወቅ እንደሚገባ ተናግረዋል። አትሌቶችም ከፖለቲካ ነፃ ሆነው ለንፁህ ስፖርት ያላቸውን ወገንተኝነት ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል። በኦሊምፒክ መድረክ መሰል ተቃውሞና መልዕክት ማስተላለፍ እንደማይቻል የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባለፈው ወር ሉዛን ላይ በነበረው ስብሰባም ሃሳብ መነሳቱ ይታወሳል። ይሁን እንጂ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች የፖለቲካ ተቃውሞ፣ የሃይማኖትና የዘረኝነት መልዕክቶች በአትሌቶች በኩል ሲተላለፉ ማየት እየተለመደ መጥቷል። በተሸኘው 2019 የፈረንጆች ዓመት እንኳን በሃያ አራት ሰዓት ልዩነት ውስጥ አሜሪካውያን አትሌቶች በፓን አሜሪካን ጨዋታዎች የፖለቲካ ተቃውሞ በስፖርት መድረክ ሲያደርጉ በዓለም የውሃ ዋና ቻምፒዮና ወቅት አውስትራሊያዊው አትሌት ማክ ሆርተንና እንግሊዛዊው ዱንካን ስኮት ቻይናዊው ሰን የንግ አበረታች መድኃኒት ተጠቃሚነት ጋር ተያይዞ ስሙ የሚነሳ በመሆኑ በአንድ ላይ ቆመው ሽልማት አንቀበልም ማለታቸው መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የአትሌቶች ኮሚሽን ሊቀመንበር ኪርስቴይ ኮቬንትሪ ባለፈው ጥቅምት ወር በርካታ አትሌቶች ኦሊምፒክ መድረክ ላይ የፖለቲካ ተቃውሞ ለማድረግ ተገቢው ቦታ መሆኑን እንደሚያምኑ በመናገር የአትሌቶቹን ሃሳብ መደገፋቸው በዓለም አቀፉ ኮሚቴ ውስጥ የተከፋፈለ ሃሳብ እንዳለ አሳይተዋል። ይህንንም ተከትሎ አትሌቶች በኦሊምፒክ መድረክ የፖለቲካ ተቃውሞ ማድረግ፣የሃይማኖትና የዘረኝነት መልዕክ ማስተላለፍ አለባቸው የለባቸውም የሚለው ሃሳብ አከራካሪ ሆኖ ቆይቷል። በታሪክ አጋጣሚ ግን አትሌቶች በተለያዩ ዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች የፖለቲካም ይሁን ሌሎች መልዕክቶች ማስተላለፍ የተለመደና አሁንም ድረስ ያለ ተግባር ነው። ከቅርብ ጊዜ ክስተቶች ስንነሳ የኦሊምፒክ የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤቱ አሜሪካዊ አትሌት ፌንሰር ኢምቦደን በሽልማት ላይ እያለ የአሜሪካን ብሔራዊ መዝሙር ሲዘመር በአንድ እግሩ ተንበርክኮ በአሜሪካን ስደተኞች ላይ የሚፈጸም እንግልት፣ ዘረኝነትና የጦር መሣሪያ ዝውውርን በተመለከተ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያላቸውን አቋም ተቃውሟል። የመዶሻ ወርዋሪዋ ዌን ቤሪም በተመሳሳይ የስፖርት መድረክ የሜዳሊያ ሽልማት ሥነሥርዓት ወቅት የቀኝ እጇን ከፍ አድርጋ የአሜሪካን መንግሥት ላይ ተቃውሞ አሳይታለች። በዚህም የአሜሪካ ኦሊምፒክና ፓራሊምፒክ ኮሚቴ ሁለቱን አትሌቶች ለጥያቄ ያቀረባቸው ሲሆን ሌሎች አትሌቶችም የቶኪዮ ኦሊምፒክን ጨምሮ በሌሎች ውድድሮች ከተመሳሳይ ድርጊት እንዲቆጠቡና ድርጊቱን ፈፅመው ከተገኙ ከባድ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው አሳስቧል። ወደ አገራችን አትሌቶች ስንመጣ በሪዮ 2016 ኦሊምፒክ የተፈጠረውን አጋጣሚ የስፖርት ቤተሰቡ አሁንም ድረስ ያስታውሰዋል። አትሌት ፈይሳ የኦሊምፒኩ የመዝጊያ ውድድር በነበረው የወንዶች ማራቶን ላይ በመሳተፍ የብር ሜዳልያ ለመጎናፀፍ ሲበቃ ርቀቱን በ2፡09፡54 ሰዓት በማጠናቀቅ ነበር። በዕለቱ አርባ ሁለት ኪሎ ሜትሩን ከኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ቀጥሎ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁን ሲያረጋግጥ መላው ዓለም ባልጠበቀው ሁኔታ፤በወቅቱ በአገራችን የነበረውን የፖለቲካ ሥርዓት በመቃወም እጆቹን አጣምሮ ተቃውሞውን በመግለጽ የዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙኃን ትልቅ የመነጋገሪያ ርዕስ መሆን ችሏል። ከዚያም በኋላ በሰጣቸው መግለጫዎች ይህን አቋሙን ደጋግሞ አንፀባርቋል። እጆቹን አጣምሮ ከፍ በማድረግ የተቃውሞውን ምልክት ካሳየ በኋላ ወደ አገር ቤት ሳይመለስም ቀርቷል።በወቅቱ የነበሩ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ፈይሳ ወደ ሀገር ቤት ቢመለስ ምንም ዓይነት ችግር እንደማይገጥመው ቢገልፁም እርሱ ግን ለመመለስ አልፈቀደም ነበር። ሌታስ ራን በተባለው ታዋቂ የአትሌቲከስ ድረገፅ የቀረበ አንድ አስተያየት ፈይሳ ሌሊሳ በአሜሪካ ተወዳጅነት እያገኘ መምጣቱን ጠቅሶ ያነሳው አጀንዳ ነበር። ፈይሳ አሜሪካ ከገባ በኋላ የተለያዩ መግለጫዎችን ለአሜሪካ እና ለሌሎች ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሰጥቷል። በእነዚህ መግለጫዎች የተቃውሞ ምልክቱን በተደጋጋሚ ከማሳየቱም በላይ የዓለም ግዙፍና ተጽዕኖ ፈጣሪ መገናኛ ብዙኃን ትኩረትን ማግኘት ችሏል። የዋሽንግተን ፖስት የአፍሪካ ቢሮ ኃላፊ ‹‹የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ ብልህ ተግባር›› ብሎ አደነቀው። ከዚያም በኋላ የቢቢሲ ጋዜጠኛ የኦሊምፒኩ እጅግ አስደናቂ ክስተት ብሎ አስተያየት ሰጠበት። አልጄዚራና ሌሎችም ታላላቅ መገናኛ ብዙኃን «ብልሁና ጀግናው ኦሊምፒያን» በማለት አሞካሽተውታል። በአሜሪካዋ የሲያትል ከተማ የሚንቀሳቀሰው የአፍሪካ አትሌቶች ማህበር በየዓመቱ የሚያካሂደውን የ5ኪሜ የጎዳና ላይ ሩጫውን በፈይሳ ሌሊሳ ጀግንነት ሰይሞታል።በ1968 እአአ ላይ በሜክሲኮ ኦሊምፒክ ላይ ሁለት ጥቁር አሜሪካውያን አትሌቶች ቶሚ ስሚዝ እና ጆን ካርሎስ ካሳዩት የተቃውሞ አቋም ጋር እሱም ባለታሪክ ሆኖ እየተጠቀሰ ቆይቷል። ሁለቱ ጥቁር አሜሪካዊ አትሌቶች በ200 ሜትር እንደቅደም ተከተላቸው የወርቅ እና የነሐስ ሜዳልያ ከተሸለሙ በኋላ በሜዳልያ ሽልማት ሥነሥርዓት ላይ የአሜሪካ መዝሙር ሲዘመር የብላክ ፓወርን የሚያንፀባርቅ ክንዳቸውን አሳይተው ነበር። በዚህ ተቃውሟቸው ሁለቱም ሜዳልያቸውን ተነጥቀዋል። ሁለቱ ኦሊምፒያኖች በወቅቱ በሽልማት ሥነሥርዓቱ ላይ ተቃውሟቸውን ክንዳቸውን በማንሳት ሲገልፁ አንድ አንድ እጃቸው ላይ ጥቁር ጓንት አድርገው፤ ጥቁር ካልሲዎች ያለጫማ አድርገው የነበረ ሲሆን በጊዜው ተንሰራፍቶ የነበረውን ዘረኝነት በመቃወም ያደረጉት ነው። ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ በዘረኝነት ላይ የተቃውሞ ተግባር ማሳየታቸውን አውግዞ ቅጣት አስተላልፎባቸዋል። ሁለቱ ጥቁር አሜሪካዊ ኦሊምፒያኖች ሜዳልያዎቻቸውን ቢነጠቁም በትውልዳቸው ጀግኖች ነበሩ። በሳንሆዜ ሐውልት የቆመላቸው ሲሆን ዘጋቢ ፊልሞችም ተሰርቶላቸዋል። የኦሊምፒክ ቻርተር አንቀፅ 50 መሠረት በኦሊምፒክ መድረክ ማናቸውንም ዓይነት የፖለቲካ አጀንዳ፤ ተቃውሞ ወይንም ተግባር የማይፈቀድ እና የሚያስቀጣ መሆኑን ይደነግጋል። አዲስ ዘመን ጥር 2/2012 ዓ.ም ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=25498
[ { "passage": "እአአ\nበ1980 ሞስኮ ባዘጋጀችው ኦሊምፒክ፤ የ5ሺ ሜትር አሸናፊ ኢትዮጵያዊው አትሌት ምሩጽ ይፍጠር መሆኑ ለዓለም አዲስ ታሪክ ነበር። ምክንያቱ ደግሞ በዘመናዊው ኦሊምፒክ ከዚያ ቀደም በተካሄዱት 14 መድረኮች አንድም አፍሪካዊ የወርቅ ሜዳሊያ ሳያጠልቅ መቆየቱ ነው። ርቀቱ በበላይነት የተያዘውም በአውሮፓውያን አትሌቶች ሲሆን፤ በተለይ ፊንላንዳውያን በርቀቱ ነግሰው እንደነበር ታሪክ ያወሳል። በ10ሺ ሜትርም በተመሳሳይ የበላይነቱ በአውሮፓውያን አትሌቶች (ለ11 ኦሊምፒኮች) የተያዘ ነበር። እአአ በ1968 ኬንያዊው ናፍታሊ ተሙ እና ኢትዮጵያዊው ማሞ ወልዴ ተከታትለው የወርቅና ብር ሜዳሊያውን እስኪወስዱት ድረስ። የምስራቅ አፍሪካውያኑ አትሌቶች ድል አድራጊነቱን ከተቀላቀሉ በኋላም የደረጃ ሰንጠረዡን ቀዳሚ ስፍራ ሊቆጣጠሩት ችለዋል። ከኦሊምፒክ ባሻገር ባሉ ውድድሮች ላይ የሚታየው ልምድም ከዚህ የተለየ የሚባል አይደለም። ኢትዮጵያ\nለዘመናት ስሟን ያስጠራችበት ይህ የአትሌቲክስ ውድድር ግን ለመጥፋት ጥቂት ቀርቶታል። በርካታ ጀግና አትሌቶች ድል የነሱበት የ10ሺ ሜትር ርቀት በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እንዲሁም በኦሊምፒክ ብቻ ከተወሰነ ሰነባብቷል። በዳይመንድ ሊግ ይታይ የነበረው የ5ሺ ሜትር ርቀትም ተመሳሳይ ዕጣ እንደሚደርሰው ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በቅርቡ አስታውቋል። ከጥቂት\nአስርት ዓመታት ወዲህ ሙሉ ለሙሉ በምዕራባውያኑ የበላይነት ተይዞ የቆየው ርቀት በምስራቅ አፍሪካውያኑ አትሌቶች ተወስዷል። ሀገራቱ በዚህ ምክንያት ሙሉ ትኩረታቸውን ወደ አጭርና መካከለኛ ርቀቶች እንዲሁም የሜዳ ላይ ተግባራት እንዲያደርጉም ተገደዋል። ስለዚህም በአፍሪካውያን የተወሰደ ክብራቸውን ለማስመለስ ሀገራትን ማዳከም የመጀመሪያው እርምጃቸው መሆኑ ጸሃይ የሞቀው ሃቅ ነው። ውሳኔውን ተከትሎም በርቀቱ በተለይ ውጤታማ የሆኑት ጎረቤታሞቹ ኬንያ እና ኢትዮጵያ ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ። ምንም እንኳን በኬንያ በኩል የመወላወል ነገር እየታየ ቢሆንም፤ ኢትዮጵያ ግን በፌዴሬሽኗ፣ በኦሊምፒክ ኮሚቴዋ እንዲሁም በዝነኛ አትሌቶቿ ትግል ማድረጓን ተያይዛዋለች። መታገሉ በህዝቡ ዘንድ እንደ ባህል የሚታየውን ውድድር ወደ ቀድሞ ክብሩ እንዲመለስ ለማድረግ መልካም ሆኖ ሳለ፤ ሌላ የቤት ስራ የሚሰጥ መሆኑ ግን መዘንጋት የለበትም። ይህም ኢትዮጵያን ለመሳሰሉ ሀገራት ይታወቁበት ከነበረው ርቀት ሌላ አማራጭ እንዲመለከቱ የግድ የሚል መሆኑን ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በረጅም ርቀት አትሌቲክስ የተጣለውን ውሳኔ ከማስቀልበስ እንቅስቃሴው ባሻገር በሌሎች ርቀቶች ላይ የሚገኙአትሌቶችን መመልከት ይኖርበታል። በተለይ ለአጭር ርቀት እንዲሁም ለሜዳ ላይ ተግባራት ምቹ የሆኑ የአካል ብቃት እንዲሁም የአኗኗር ሁኔታ ላይ በሚገኙ አትሌቶች ላይ ትኩረቱን መጨመር እንደሚገባው በትክክልም የሚጠቁም ነው። በውሳኔው\nመሰረት በረጅም ርቀት የሚካፈሉ አትሌቶች ሁለትና አራት ዓመታትን ጠብቀው መወዳደራቸው የግድ ነው። የፌዴሬሽኑ ስጋት ደግሞ አትሌቶች ዓመታትን ከመጠበቅ ይልቅ ፊታቸውን ወደ ጎዳና ሩጫዎች መመለሳቸው ይጎዳቸዋል የሚል ነው። ይህ ስጋት ትክክለኛ ቢሆንም ግን ከማራቶን ባሻገር በመካከለኛ፣ በአጭር፣ በዝላይ፣ በውርወራ እንዲሁም በእርምጃ ወደ ሚካሄዱ ውድድሮች ፊታቸውን እንዲያዞሩ ማድረግ ተገቢ ነው። ኢትዮጵያ ከኬንያ ስትነጻጸር በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ ሜዳሊያ ያስመዘገበችው፤ በ1ሺ 500 ሜትር፣ በ3ሺ ሜትር መሰናክል፣ በ5ሺ ሜትር እንዲሁም በ10ሺ ሜትር ውድድሮች ብቻ ነው። በአንጻሩ ኬንያ ከእነዚህ ርቀቶች ባሻገር በ400 ሜትር፣ በ400 መሰናክል፣ በ400 ሜትር፣ 800 ሜትር እንዲሁም በጦር ውርወራ ሜዳሊያ ማግኘት ችላለች። ይህም ኢትዮጵያ ምን ያህል በአንድ አካባቢ ተወስና እንደቀረች የሚያሳይ ሲሆን፤ ኬንያ በበኩሏ ተሳትፎዋን በማብዛቷ ውጤታማ ለመሆኗ ማሳያ ይሆናል። ኢትዮጵያም ሁሌም ከምትነሳባቸው አራትና አምስት ርቀቶች ያላለፈ ዝናዋን በድጋሚ መገንባት የሚቻልበት መንገድ መኖሩን መዘንጋት አያስፈልግም። ለፌዴሬሽኑ እንዲሁም ለኦሊምፒክ ኮሚቴም አካባቢያቸውን እንዲቃኙ በግልጽ የተቀመጠ ማንቂያ ይሆናል። እንደ ነባራዊው ሁኔታ ከሆነ፤ በኢትዮጵያ ባሉ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ከወረዳ ጀምሮ አያሌ የታዳጊ ወጣት ፕሮጀክቶች ይገኛሉ። በእነዚህ ፕሮጀክቶችም ከእግር ኳስ ስፖርት በሚስተካከል መልኩ የአትሌቲክስ ስፖርት ስልጠና ይሰጣል። ከዚህ ባሻገር በሀገር አቀፍ ደረጃ አራት የስልጠና ማዕከላት እንዲሁም ሁለት አካዳሚዎች ይገኛሉ። በእነዚህም ውስጥ አትሌቲክስ በከፍተኛ ትኩረት ስልጠና የሚሰጥበት ዘርፍ ነው። በተለያዩ አካባቢዎችም በራሳቸው ጥረት እንዲሁም በግል አሰልጣኞች አትሌት ለመሆን የሚታትሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ታዳጊና ወጣቶች ይገኛሉ። ከእነዚህ\nሰልጣኞች የሚልቁት ደግሞ ትኩረታቸውን በረጅም ርቀት አትሌቲክስ ላይ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በማትታወቅበት የሜዳ ላይ ተግባራት ያለው ሁኔታ፤ በፍላጎት፣ በግብዓት እንዲሁም በቁሳቁስ እጥረት እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። ነገር ግን በተለያዩ ጊዜያት ፌዴሬሽኑ ባደረገው ምልከታም ይሁን ባለሙያዎች እንደሚገልጹት በተለይ በአጭር ርቀት፣ ውርወራ እና ዝላይ ውጤታማ መሆን የሚችሉ ታዳጊዎች የሚፈሩባቸው አካባቢዎች ይገኛሉ። በመሆኑም ማሰልጠኛ ማዕከላት ከእነዚህ አካባቢዎች ወጣቶችን በመመልመል፣ ፌዴሬሽኑም አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት እንዲሁም ተገቢውን ስልጠና እንዲሰጥ በማድረግ ውጤታማነትን መመለስ ይችላል። የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከዓመት በፊት በመላ ሀገሪቷ በዚህ ጉዳይ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ምልከታ በባለሙያዎቹ ማድረጉ የሚታወስ ነው። ስልጠናው የሚሰጥባቸው ቦታዎች ከባህር ጠለል በላይ የሚገኙበትን በመመልከት እንዲሁም የአኗኗር ሁኔታቸውን በማጥናት ለየትኛው የስፖርት ዓይነት ምቹ ነው የሚለውንም ለይተዋል። በወቅቱ ፌዴሬሽኑ ባስቀመጠው ስታንዳርድ መሰረት አዳዲስ አትሌቶችን የመመልመል ስራዎች መሰራታቸውን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ አስታውቀው ነበር። በአቅርቦት ላይ የሚታየውን ችግር ለመፍታትም ፌዴሬሽኑ በአነስተኛ ዋጋ ከሚያቀርቡ ከሀገር ውስጥ አምራች ድርጅቶች ጋር በመነጋገር ላይ መሆኑ ተጠቁሞ ነበር። በተለይ እንደየ ሰልጣኙ እድሜ፣ ለውድድርና ለስልጠና በምን ያህል መስፈርት መዘጋጀት ይገባል እንዲሁም ለየክልሎቹ ምን ያህል አቅርቦት ያስፈልጋል በሚለው ላይም ፌዴሬሽኑ ዝግጅት ተደርጓል። በሀገሪቷ\nያሉት አሰልጣኞች ቁጥር ከስልጠናውና ከሰልጣኞቹ ጋር የሚመጣጠን አለመሆኑም ተረጋግጧል። በመፍትሄነትም አሰልጣኞችን ከውጭ ሀገራት ለማስመጣት መታቀዱ በወቅቱ ተገልጾ ነበር። ልምድ ያላቸውን አሰልጣኞች ለማስመጣት በሙከራ መሆኑንና ለኢትዮጵያውያን አሰልጣኞች ልምድና ተሞክሮዎችን እስደሚሰጡም ይጠበቅ ነበር። ይህንን\nስራ ቀድሞ የመጀመሩ አስፈላጊነት አያጠያይቅም፤ ነገር ግን ቀጣይነቱ ላይ ምን እየተሰራ ይገኛል? የሚለው ዋነኛው ጉዳይ ነው። በፌዴሬሽኑ በኩል በዓለም ላይ እየታየ ያለውን ሁነት ተከትሎ መፍትሄ ማበጀት እንዲሁም የጀመሩትን ስራ ከዳር ማድረስ የግድ መሆኑም መዘንጋት የለበትም። ከጥያቄው ባሻገር የተሰጠውን የቤት ስራ ለማከናወን በሙሉ ዝግጁነት መነሳትም አስፈላጊ ነው።", "passage_id": "127551a136af260b2579d72e99514d08" }, { "passage": "ጎረቤታሞቹ የምስራቅ አፍሪካ የረጅም ርቀት ፈርጦች ኬንያና ኢትዮጵያ በአትሌቲክሱ ያላቸውን መልካም ስም ያህል በስፖርቱ ትልቅ አደጋ እያንዣበበባቸው ይገኛል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአትሌቲክሱ አበረታች መድሃኒት ወይም ንጥረ ነገሮች ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ ሩሲያንን የመሳሰሉ ታላላቅ አገራት ከታላላቅ ውድድሮች እስከመታገድ ደርሰዋል። እነዚህ አገራት አትሌቶቻቸው በብዛት አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆነው ከመገኘታቸው ጋር ተያይዞ በመንግስት ጭምር ይደገፋሉ በሚል ከውድድሮች መታገዳቸው ይታወቃል። የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ኤጀንሲ እነ ሩሲያን በቀጣበት ወቅት ኢትዮጵያና ኬንያ አደጋው በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሰጋቸው በማሳወቅ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ምክረሃሳብ ሰጥቷቸው ነበር። ሁለቱ አገራት በተለይም ኢትዮጵያ ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥታ በመስራት አበረታች ውጤት ማስመዝገቧም በኤጀንሲው ጭምር ተመስክሮላታል። ያም ሆኖ ስጋቱ ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ለማለት አይቻልም። ባለፈው ዓመት የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያና ኬንያን በአበረታች መድሃኒት(ዶፒንግ) ምክንያት ስጋት ካለባቸው አገራት ቀዳሚውን ደረጃ እንደሚይዙ ማሳወቁ ይታወሳል። ዘንድሮም ሁለቱ አገራት በአበረታች መድሃኒት ስጋት ቁንጮውን ደረጃ መያዛቸው እንደማይቀር እየወጡ ያሉ መረጃዎች ጠቋሚ ናቸው። ለዚህም ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ አምስት የአፍሪካ አገራት አትሌቶች አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆነው መገኘታቸው ማሳያ ተደርጓል። ቤላሩስና ዩክሬን ሁለቱን የአፍሪካ አገራት ተከትሎ ስማቸው ከቁንጮዎቹ ተርታ ተፅፏል። የአስራ ስምንት ዓመቷ ኬንያዊት አትሌት አንጌላ ሙንጉቲ ከቀናት በፊት አበረታች መድሃኒት ተጠቅማ በመገኘቷ እገዳ ተጥሎባታል። በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የስምንት መቶ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊ የሆነችው ይህች አትሌት በዚህ ወንጀል የተያዘች አርባ አራተኛዋ ኬንያዊት አትሌት ሆናለች። አትሌቷ ባለፈው ዓመት አርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደው የወጣቶች ኦሊምፒክም በስምንት መቶ ሜትር አገሯን ወክላ መወዳደር ችላለች። የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች መድሃኒት አዋጅ የትኛውም አትሌት በውስጡ ለተገኘ አበረቻች ንጥረ ነገር ሃላፊነቱን ይወሳዳል። ይህችም አትሌት ኖራንድሮስቴሮን የተባለ አበረታች ንጥረነገር ተጠቅማ መገኘቷ ተረጋግጣል። ሙንጉቲ በስምንት መቶ ሜትር 2፡06፡21 የሆነ የራሷ ፈጣን ሰዓት ያላት ሲሆን ባለፈው ዓመት በኬንያ ከሃያ ዓመት ቻምፒዮና ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቅ ችላለች። ፊሊፕ ሳንጋ ኪሙታይ የተባለው የሰላሳ ስድስት ዓመት ኬንያዊ አትሌት ቴስቴስትሮን የተባለ አበረታች ንጥረነገር ተጠቅሞ የተገኘ አርባ ሦስተኛው ኬንያዊ አትሌት ነው። የዚህ አትሌት ምርመራ በሂደት ላይ ሲሆን ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ከስፖርቱ ለአራት ዓመታት ሊታገድ እንደሚችል ታውቋል። ኪሙታይ በማራቶን 2፡06፡07 ሰዓት ያለው ሲሆን እኤአ 2011 ላይ በፍራንክፈርት ማራቶን ያስመዘገበው ይህ ሰዓት በውድድር ዓመቱ አስራ ሦስተኛው ፈጣን አትሌት አድርጎት ነበር። ይህ አትሌት ባለፈው ዓመት በጎልድ ኮስት ማራቶን አምስተኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ 2፡11፡44 ሰዓት ማስመዝገብ ችሏል። በሆንግኮንግ ማራቶንም አስረኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡15፡31 ሰዓት ተመዝግቦለታል። በዚህ ወር በአበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነት ቅጣት የተላለፈበት ወይንም የተገኘበት አርባ ሁለተኛው ኬንያዊ አትሌት ቪንሰንት ኪፕሴጊች ነው። ይህ የሰላሳ ዓመት አትሌት ቀደም ሲል የተጠቀሰው ኬንያዊ አትሌት ኪሙታይ በጎልድ ኮስት ማራቶን አምስተኛ ሲያጠናቅቅ አራተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ ችሏል። 2፡09፡59 የሆነ የራሱ ፈጣን ሰዓትም አለው። ሚያዝያ ወር ላይም በቬና ማራቶን ሰባተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡10፡02 አስመዝግቧል። በተመሳሳይ ከዓመት በፊት በሆኖሉሉ ማራቶን ሦስተኛ ሆኖ ጨርሷል። ኢትዮጵውያን አትሌቶች በተለይም በግል ውድድሮች ብቻ የሚታወቁት አልፎ አልፎ በአበረታች መድሃኒት ሲቀጡ ይታያል። ይሁን እንጂ አገርን ወክለው በሚወዳደሩ አትሌቶች ይህ ቅሌት አይታይም ማለት ይቻላል። ባለፈው ክረምት በሞሮኮ ራባት በተካሄደው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን ወክሎ በአስር ሺ ሜትር ወርቅ ማጥለቅ የቻለው ብርሃኑ ፀጉ ኢፒኦ የተባለ ንጥረ ነገር ተገኝቶበት ላልተወሰነ ጊዜ ከስፖርቱ ታግዷል። ይህ የሃያ ዓመት አትሌት ባለፈው ወር በኮፐንሃገን ግማሽ ማራቶን ላይ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል። ብርሃኑ ሔንግሎ በተካሄደው የዓለም ቻምፒዮና የኢትዮጵያውያን ማጣሪያ ውድድር ላይ 10ሺ ሜትሩን 27፡00፡73 በሆነ ሰዓት ማጠናቀቅ ችሏል። ብርሃኑ በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ሲያሸንፍ ኤርትራዊው አሮን ክፍሌና ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ጀማል ይመር ተከትለውት መግባታቸው ይታወሳል። ብርሃኑ የወርቅ ሜዳሊያውን ተነጥቆ ለኤርትራዊው አትሌት፣ የብር ሜዳሊያው ደግሞ ለጀማል ይመር የሚሰጥ ሲሆን አራተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ኬንያዊው ኤድዊን ሦይ የነሐስ ሜዳሊያ ሊያገኝ እንደሚችል መረጃዎች እየወጡ ነው። በአዲስ አበባ አበረታች መድሃኒቶች በስቴድየም አካባቢ ካለ ሃኪም ማዘዣ ጭምር እንደሚሸጡ የእንግሊዝ ሚዲያዎች መዘገባቸውን ተከትሎ የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያን ማስጠንቀቁ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ፅሕፈት ቤትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቶች የተለያዩ ትምህርቶችን እየሰጡ ይገኛሉ። በቅርብ ወራት አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆኖ በመገኘት ስማቸው ከተዘረዘሩ አፍሪካውያን መካከል ሞሮኳዊው ሙስጠፋ ኤል አዚዝ አንዱ ነው። ይህ አትሌት ለአራት ዓመታት ከስፖርቱ እንዲርቅ ቅጣት የተጣለበት ሲሆን 2014 የአፍሪካ ቻምፒዮና ላይ በአስር ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ በማጥለቁ ይታወቃል። ይህ የሰላሳ ሦስት ዓመት አትሌት ባለፈው ሰኔ ክሮሽያ ውስጥ በተካሄደ የጎዳና ላይ ውድድር አበረታች ንጥረነገር ተጠቅሞ በመገኘቱ እገዳው እንደተላለፈበት ተነግሯል። ሞሮኮ በአበረታች መድሃኒት አደጋ ውስጥ ከሚገኙ አገራት መካከል ትጠቀሳለች። ይሁን እንጂ በዚህ አደጋ እጅግ ችግር ውስጥ ካሉ አገራት ተርታ በ2017 የወጣች ቢሆንም አሁን ተመልሳ ገብታበታለች።አዲስ ዘመን ጥቅምት 17/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "7c84ac503336f93af8e8b10eea9d4592" }, { "passage": "ይህ ዓመት እንደ ከዚህ ቀደሞቹ ቢሆን፤ በስፖርቱ ዓለም በተለይ በዚህ ወቅት በርካታ ውድድሮች፣ ጉባኤዎችና ሥልጠናዎች ሊካሄዱ ይችሉ ነበር። ነገር ግን ሳይታሰብ ተከስቶ ዓለምን ባዳረሰው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ወረርሽኝ ምክንያት ውድድሮች ብቻም ሳይሆኑ በርካታ ጉዳዮች በታቀደላቸው ሁኔታ እንዳይካሄዱ ማድረጉ ግልጽ ነው። ታዲያ የስፖርት ማህበራትና ሌሎች ተቋማት እቅዶቻቸው በዚህ መልኩ አቅጣጫቸውን ሲስቱ ምን ዓይነት አማራጮችን ተጠቀሙ? ከዓመት እስከ ዓመት በሩጫ ላይ ከሆኑና በሥራ ከሚወጠሩ ፌዴሬሽኖች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ነው። የፌዴሬሽኑ የሥልጠና ጥናትና ምርምር ዳይሬክተሩ አቶ ሳሙኤል ብርሃኑ የሚናገሩት አላቸው። የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ቻምፒዮናን ጨምሮ የሻምበል አበበ ቢቂላ ማራቶን፣ የወጣቶች ቻምፒዮና እንዲሁም ሌሎች ውድድሮች ፌዴሬሽኑ በዚህ ዓመት ያላካሄዳቸው የውድድር ዘርፍ እቅዶች ናቸው። በሥልጠና ጥናትና ምርምር ዘርፍ ደግሞ የዚህ ዓመት ዋነኛ እቅድ የነበረው ባለሙያዎችን ማብቃትና መመዘን መሆኑን ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። ዳኞችና አሰልጣኞች ዓለም አቀፍ ሥልጠናዎችን አግኝተው ደረጃቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ባለበት ወቅት ግን የዓለም ትኩሳት የሆነው ጉዳይ በመከሰቱ እንደታሰበው ማስኬድ አልተቻለም ይላሉ። በተለይ ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ የሥራ ክፍሉ በዚህ ለማሳለፍ ያስቀመጠው እቅድ ወደ መሬት ሳይወርድ ቀርቷል። በዓመቱ\nኦሊምፒክና ሌሎች ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ መሳተፍና ብሔራዊ ቡድንን የማዘጋጀት እቅድም ተመሳሳይ ዕጣፈንታ ገጥሞታል። ለብሔራዊ ቡድን የተጠሩ አትሌቶችም ተበትነው ወደየ ቤታቸው ሄደዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ፌዴሬሽኑ ግን ሥራውን ከማቋረጥ ይልቅ ሌሎች አማራጮችን መጠቀምን መርጧል። ዋናው የአትሌቶች ጤንነትና በብቃት መቆየት በመሆኑም የተሻለ ያለውን ተግባር ሲከውን እንደቆየ ዳይሬክተሩ ያስረዳሉ። ፌዴሬሽኑ\nከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ስፖርታዊ ክዋኔዎችን ማካሄድ አዳጋች መሆኑን በመገንዘቡ ቀደም ብሎ ወደ ዝግጅት መግባቱን ይጠቁማሉ። አትሌቶች ሥልጠና ማቋረጣቸውን ተከትሎ ከስፖርቱ እንዳይርቁ እንዲሁም አሰልጣኞችም ከአትሌቶቻቸው በጋራ ያላቸው ግንኙነት እንዳይቋረጥ ምን ማድረግ ይገባል? የሚለውን በማሰብም ነው በቴሌቪዥን ስርጭት በትምህርትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ፕሮግራሞች እንዲተላለፉ የተደረገው። በዚህም የስፖርቱ ባለሙያዎችን በማካተት በሦስት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለስድስት ሳምንታት ለአትሌቶች ጠቃሚ የሆኑ መርሃ ግብሮች ሲተላለፉ ቆይቷል። የመርሃ ግብሩ ይዘትም ሥነ-ልቦና፣ ሥነ-ምግብ፣ ሕክምና፣ ማህበራዊ ግንኙነት፣ የተምሳሌት አትሌቶች መልዕክት፣ የአሰልጣኞች ምክረ ሃሳብ እንዲሁም አትሌቶች በአጠቃላይ ምን ማድረግ ይገባቸዋል የሚለውን ያጠቃለለ ነበር። ከቴሌቪዥን ስርጭቱ ባሻገር በፌዴሬሽኑ ይፋዊ ማህበራዊ ገጽ (ፌስ ቡክ) እንዲሁም በድረገጹ አማካኝነትም አትሌቶችን ተደራሽ ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህ\nሂደትም ፌዴሬሽኑ ማድረግ የሚገባውን መልካም ተግባር ማከናወኑን ለመታዘብ ተችሏል። አትሌቶችና ሌሎች ባለሙያዎችም ለዚህ የሚሰጡት ግብረ መልስ ጥሩ ሥራ መሰራቱን የሚያሳይ ነው። አትሌቶች ቤታቸው በሚሆኑበት ወቅት ምን መስራት እንዳለባቸው ግራ ተጋብተው ነበር የሚሉት ዳይሬክተሩ፣ አሰልጣኞች በሚሰጧቸው አቅጣጫ ተጠቃሚ ሆነዋል። በተለያዩ ክልሎች ለሚገኙና እነዚህን አማራጮች የማያገኙ አትሌቶችን ደግሞ አሰልጣኞች በስልክና በሌሎች መንገዶች በተመሳሳይ እየረዷቸው ይገኛሉ። አሁን ካለው ሁኔታ አንጻር ጥናት መስራትና አትሌቶችን ማግኘት ባይቻልም በተለያዩ መንገዶች ምስጋናቸውን ያደርሳሉ። በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክር የሚጠይቁ አትሌቶች ቁጥር መበራከትም ይህንኑ የሚያመላክት ነው። አሰልጣኞች በበኩላቸው ወትሮ ከነበረው ሁኔታ በተሻለ መልኩ ከፌዴሬሽኑ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ያጠናከሩ ሲሆን፤ ግብረመልስ በመስጠትም አጋርነታቸውን እያሳዩ ነው። ከዚህ\nበኋላም ፌዴሬሽኑ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት ጎን ለጎን መርሃ ግብሩን በአዲስ መልክ የሚያስቀጥልም ይሆናል። የሀገርን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያስጠራው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በሚደረገው ርብርብ ቅድሚያ ተሰላፊ መሆኑን በተግባር በማሳየት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። ከዚህ ቀደም በግሉ፣ ከሌሎች ተቋማት ጋር እንዲሁም በአትሌቶቹ አማካኝነት በገንዘብ እንዲሁም በቁሳቁስ የድርሻውን በማድረግ ላይ ይገኛል። አመራሩና ሌሎች ታዋቂ አትሌቶችም ለሕዝቡ መልዕክት በማስተላለፍ ላይ ናቸው። አሁንም ከዚህ በላቀ መልኩ ለመስራት የሚያስችል ተነሳሽነት አለ። እንደሚታወቀው\nበዚህ ወቅት ውድድሮችና ሌሎች የሥልጠና መርሃ ግብሮች ተቋርጠዋል። በዚህ ምክንያት ፌዴሬሽኑ ቀድሞ የያዛቸውን እቅዶች በመቀየር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሮች ላይ ለማተኮር ማቀዱን ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። በዚህም ከፌዴሬሽኑ ስፖንሰር ማልታ ጊነስ ጋር በመሆን በቴሌቪዥን የሚተላለፉ መርሃ ግብሮችን በመስራት ላይ ነው። በአንድ ወር ውስጥ ለ16 ቀናት ያህል የሚተላለፈው መርሃ ግብሩ እንደ ቀድሞ በምክረ ሃሳብ ላይ ሳይሆን በተግባር ላይ የተመሰረተ እንደሚሆንም ታውቋል። በአትሌቶች ዘንድ ተምሳሌት የሆኑና ዝነኛ አትሌቶች እንዲሁም ባለሙያዎች የሚሳተፉበት ሲሆን፤ ተከታታይነት ያላቸው እንቅስቃሴዎች በምን መልኩ እንደሚሰሩ የሚያሳይም ይሆናል። እንቅስቃሴው ከአትሌቶች ጋር ብቻ ሳይሆን ሌላውን ኅብረተሰብም የሚጠቅምም ነው የሚሆነው። ለዚህ የሚሆነው ዝግጅት በመጠናቀቁ በቅርቡ አየር ላይ የሚውልም ይሆናል። በዚህ\nወቅት አብዛኛው ኅብረተሰብ ትኩረቱ የመገናኛ ብዙኃን ላይ በመሆኑ፤ ትብብራቸውን እንዳያቋርጡ ይጠይቃሉ። ከቴሌቪዥን ባሻገር በርካቶችን ተደራሽ የሚያደርጉ የመገናኛ ብዙኃን አብሮነታቸውን እንዲያሳ ዩም ጠይቀዋል።አዲስ\nዘመን ግንቦት 19/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "66e0e14f27a08cecb713d5ae9e964fe9" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳ በኢትዮጵያ ስፖርት፤ ማህበራትና ክለቦች ከመንግስት እገዛ አለመላቀቃቸውና ሃብት በማመንጨት ተግባር ላይ ተሳታፊ አለመሆናቸው እንደ ድክመት ይነሳል።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአጭር ጊዜ ውስጥ ፕሪሚየር ሊጉ በአክሲዮን ማህበር እንዲተዳደር በማድረግና ከጥገኝነት እንዲላቀቅ የማድረጉ ጅማሬም መልካም የሚባል ነው።ስፖርቱን በበላይነት በሚመራው ብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤትም የፌዴሬሽኑ ተግባር ለሌሎች ስፖርት ማህበራትም አርአያነት ያለው መሆኑ በሪፖርት ቀርቧል።ይሁን እንጂ ስፖርቱ በገቢ ረገድ ችግር እየደረሰበት መሆኑ ነው ፌዴሬሽኑ የጠቆመው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ\nፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ\nጂራ በመድረኩ ላይ\n፤ እግር ኳሱ\nበስፖንሰር ምክንያት እየደረሰበት\nያለውን ችግርና ችግሩ\nየተፈጠረበትን ምክንያት መንግስት\nማጤን ይኖርበታል ሲሉ\nገልጸዋል።ይኸውም በህዝብ ተወካዮች\nምክር ቤት የወጣውን\nየአልኮል መጠጦች ማስታወቂያ\nበህዝብ መገናኛ ብዙሃን\nእንዳይተላለፍና በስታዲየሞች \n ውስጥ እንዳይሰቀል የሚከለክለው አዋጅን በቀጥታ እግር ኳሱን የጎዳ መሆኑን ይጠቁማሉ።በእርግጥ መንግስት ዜጎቹን የመጠበቅ ኃላፊነት ይኑርበት እንጂ መታየት ያለባቸው ጉዳዮች ሳይመዘኑ ታልፈዋል የሚሉት አቶ ኢሳያስ፣ ‹‹ጉዳት አድርሶብናልና ቢፈተሽ›› ሲሉ ጥያቄያቸውን ለብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤቱ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ፌዴሬሽኑ ባለፈው ዓመት ከዋሊያ ቢራ ጋር 56 ሚሊየን ብር የስፖንሰር ስምምነት አድርጎ ነበር፤ ነገር ግን ይህ አዋጅ በወጣ ማግስት ስምምነቱ ተቋርጧል።በዓለም ላይ በሃብቱ ቀዳሚ የሆነው የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ በሃይንከን ቢራ ስፖንሰር እንደሚደረግ ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፤ ሌሎች ሊጎችም በመጠጥ አምራች ተቋማት ስፖንሰር የሚደረጉበት አሰራር በዓለም ላይ የተለመደ መሆኑን ጠቁመዋል።ፌዴሬሽኑ በዚህ ረገድ ያለውን ሃሳብ በጽሁፍ ለመንግስት ማቅረቡንና አዋጁ በፌዴሬሽኑ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረሱ በድጋሚ እንዲፈተሽ ካልሆነም መንግስት ብሄራዊ ቡድኖችን እንዲደግፍ ጠይቀዋል። እንደ ፕሬዚዳንቱ ማብራሪያ፤\nችግር ሲያጋጥም እርዳታ\nከማድረግ ባለፈ በኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን ስር\nካሉ የስፖርት ማህበራት\nመካከል ምንም ዓይነት\nድጋፍ ከማይደረግላቸው መካከል\nአንዱ የኢትዮጵያ እግር\nኳስ ፌዴሬሽን ነው።ፌዴሬሽኑ\nበስሩ ያሉትን ሰባት\nብሄራዊ ቡድኖችን (በሁለቱም\nጾታ በተለያየ የዕድሜ ክልል እና ዋናውን ቡድን ጨምሮ) በራሱ ነው የሚያስተዳድራቸው።ካሜሩን ለምታዘጋጀው የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን(ዋሊያዎቹ) ከማዳጋስካር፣ ኒጀር እና ኮት ዲቭዋር ጋር ተደልድሏል።በመሆኑም ቡድኑ የጉዞ፣ የሆቴልና ሌሎች በርካታ ወጪዎችን ማድረጉ የግድ ነው።በተመሳሳይ ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከዚምቧቡዌ እና ከጋና ጋር ባላት ድልድል ሌሎች ወጪዎችን ማድረግም ይጠይቃል።ሌሎቹ ብሄራዊ ቡድኖችም ለሚኖሯቸው አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ጨዋታዎች ተጨማሪ ወጪዎች ይጠበቃሉ።መንግስት ይህንን በባለቤትነት ወስዶ ብሄራዊ ቡድኖችን ሊያግዝ ይገባዋል። ብሄራዊ ቡድን ሃገር የምትወከልበት መሆኑ መንግስት ሊደግፈው ይገባሉ ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚካፈለው የአትሌቲክስ ቡድን በመንግስት እገዛ እየተደረገለት መሆኑን በማሳያነት ይጠቅሳሉ።ይህ የስፖርት ማህበራት ድክመት ደግሞ ብሄራዊ ቡድኑንም ደካማ አድርጎታል፤ በመሆኑም መንግስት ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል። አብዛኛዎቹ የእግር ኳስ ክለቦች የሚተዳደሩት በመንግስት እንደመሆኑ፤ ፌዴሬሽኑ ደግሞ ይህ መንግስት የሚመድበው ከፍተኛ ገንዘብ በዚህ መቀጠል የለበትም የሚል ሃሳብ እንደሌለው ገልጸዋል።ክለቦችን ወደ ግል ተቋም ለመመለስ በማቀድ ለሶስት ዓመታት ፕሮጀክት በመያዝ እየተንቀሳቀሱ ሲሆን፤ የመጀመሪያዎቹን ስድስት ወራት ከአንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ጋር በመሆን በትምህርት ቀጣዮቹን ጊዜያት ደግሞ 30 ከመቶ የሚሆኑትን ክለቦች 30 በመቶ መንግስት 40 በመቶ ህብረተሰቡ እንዲይዛቸው የግል ባለሃብት ተሳትፎ በማከል ሙሉ ለሙሉ ከመንግስት ለማላቀቅ ታቅዷል።በመሆኑም ምክር ቤቱ አንድ አቅጣጫ መስጠት እንደሚገባው አሳስበዋል፤ ይህ ካልሆነ ግን መንግስት ድጋፉን ቢያቋርጥ አስቸጋሪ ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ጠቁመዋል። ክልሎችም በስራቸው የሚያስተዳድሯቸው ክለቦች እንደመኖራቸው ለዚህ ስራ ተባባሪና በሚወጣው ደንብም ለመመራት እገዛ እንዲያደርጉም ፕሬዚዳንቱ ጠይቀዋል። በመድረኩ ላይ ሃሳባቸውን ያንጸባረቁት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሼር ካምፓኒ የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ፤ ባለፉት ዓመታት በሁለቱም ጾታዎች በዋናው ብሄራዊ ቡድንም ሆነ በእድሜ በተቀመጡት ቡድኖች የተደረጉት እንቅስቃሴዎች ደካማና አንገት የሚያስደፉ እንደሆኑ መታየታቸውን ይጠቁማሉ።ብሄራዊ ቡድኖች ሲያሸንፉ በተለያዩ የሃገሪቷ ከተሞች ላይ በህዝቡ ዘንድ የሚፈጠረው ተነሳሽነት ታይቷል። ሰብሳቢው አንድ ያልታተመ ጥናትን ዋቢ በማድረግ በ2011/12 ዓ.ም በስፖርቱ ወደ 2ነጥብ2 ቢሊየን ብር ወጥቷል፤ ነገር ግን ውጤት አልመጣም ይላሉ።በመሆኑም እግር ኳስ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት በዚህ መንገድ ይቀጥላል ወይስ ክለቦች ወደ ግል እንዲዘዋወሩና በገንዘብ ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ታቅዷል የሚለው መመልከት አስፈላጊ መሆኑንም ነው ሰብሳቢው ያመላከቱት። በእቅዱ ላይ ክለቦች ከመንግስት ተረጂነት ሊወጡ ይገባል በሚለው ላይ ፖሊሲ አውጥቶ ወደ ግል ይዞታነት የሚዘዋወሩበትን ስትራቴጂ መንደፍ አስፈላጊ ሲሆን፤ ተግባራዊነቱም ሊመዘን ይገባል። በዚህ ወቅት ከመንግስት ጥቂት መቋቋሚያ ቢያገኙ በአጭር ጊዜ ውስጥ ራሳቸውን የሚችሉና ከፍተኛ ደጋፊ ያላቸው ክለቦች መኖራቸውንም ሰብሳቢው ይጠቁማሉ።በመሆኑም ይህ ሊታሰብበትና በብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤቱ አቅጣጫ ሊሰጠው የሚገባ ነው ይላሉ። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ በ1990 ዓ.ም የወጣው የስፖርት ፖሊሲ ከስፖርት ማህበራትና ክለቦች አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ቀስ በቀስ ከመንግስት ድጎማ መውጣት እንዳለባቸው የሚያመላክት መሆኑን ይጠቅሳሉ።ይህንን ተከትሎ የተከናወኑ ስራዎች ቢኖሩም አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከጥቂቶቹ በቀር የተቀሩት በመንግስት የሚተዳደሩ ናቸው። ዓለም አቀፍ ደረጃቸው ሲፈተሽም፤ ከስያሜ፣ ከመዝሙር፣ ከአርማ፣… ጋር የተያያዙ ጉዳዮች መስተካከል ይገባቸዋል። ብሄራዊ ምክር ቤቱም ከዚህ ቀደም አቅጣጫ ቢያስቀምጥም ብዙም አልተሄደበትም።ክለቦቹም ከመንግስት ድጎማ በመውጣት ራሳቸውን እንዲችሉ ስልቶችን መቀየስ ይገባቸዋል።ለአብነት ያህልም የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎቹን ወደ አክሲዮን የቀየረበት መንገድ ገቢውን ከማሳደግ ጎን ለጎን የታዳጊ ቡድኖችን የያዘበት ጅማሮ የሚበረታታ ነው፡፡ ፌዴሬሽኖች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ ከማድረግ ባሻገር መንግስት በስሩ ያሉትን ከ30 በላይ ማህበራት ድጋፍ የማድረግ አቅሙ ውስን ነው።በመሆኑም ክለቦችና ስፖርት ማህበራት በራሳቸው ከሚያደርጉት ባሻገር ኮሚሽኑም ጥናት ላይ ተመስርቶ በቀጣይ የሚሄድበት መሆኑን ጠቁመዋል።  ", "passage_id": "36f13b967202258e302af2bc40e2da9c" }, { "passage": "የምሥራቅ አፍሪካውያን የባህል ስፖርት የሆነው በተለይም ለኢትዮጵያ እና ኬንያ የ10ሺ እና 5ሺ ሜትር ሩጫ ታላቅ ትርጉም ያለው ነው። ያሉበት የመልካምድር አቀማመጥና የአየር ጸባይ ለስኬት እንዳገዛቸው በባለሙያዎች ይነሳል። በግልጽ እንደሚታየው ባለፉት ዓመታት በርቀቶቹ በተካሄዱ ውድድሮች የበላይነቱን የያዙት የሁለቱ ሀገራት አትሌቶች ናቸው። ይህ ሁኔታ ደግሞ እንደ ባህል ስፖርት እንዲታይ ምክንያት ሆኗል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን በእነዚህ ርቀቶች የሚካሄዱ ውድድሮች በዓለም ላይ እየተመናመኑ መጥተዋል። የ10ሺ ሜትር ሩጫ በብቸኝነት የሚታየው በዓለም ሻምፒዮና እና ኦሊምፒክ ላይ ብቻ ሲሆን፣ በዳይመንድ ሊግ ይካሄድ የነበረው የ5 ሺ ሜትር ሩጫም ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ እንደማይካሄድ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር አስታውቋል። ይህም ሀገራቱን ያስቆጣ፤ ቅሬታዎቸውንም በማንሳት ውሳኔውን ለማስቀልበስ የተለያዩ እርምጃዎችን በመወሰድ ላይ ይገኛሉ። ባሳለፍነው ወር በዴንማርክ በተካሄደው የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ ጉዳዩን የተቃወሙት ኢትዮጵያ እና ኬንያ በተናጠል የዓለም አቀፉን ማህበር ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮን አናግረዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉም ከፕሬዚዳንቱ ጋር ቆይታ አድርጋለች። በውይይቱ ላይ ካነሷቸው ነጥቦች መካከል የ5ሺህ ሜትር ውድድር አንዱ ሲሆን በሻምፒዮናው ላይ የተካፈሉ አፍሪካውያን አትሌቶችና ደጋፊዎች የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማህበር ውሳኔን በመቃወም ድምጻቸውን አስተጋብተዋል። በሕይወት ዘመኔ መሮጥ የምፈልገውና ውጤት ለማስመዝገብ የምጓጓው በ5ሺ ሜትር ነበር ያሉት የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አትሌት ኮማንደር ማርቆስ ገነቲ፤ አገራችን የምትታወቅበት የረጅም ርቀት የአትሌቲክስ ስፖርት ከውድድር ውጪ እየሆነ መምጣቱ ልብ የሚሰብርና አሳዛኝ እንደሆነ ገልጸዋል። ነገር ግን ጉዳዩን እስከ መጨረሻው ተከታትለን የምንችለውን በማድረግ በተለይ በሚቀጥለው ዓመት የ5ሺ ሜትር ውድድር ከዳይመንድ ሊግ ውጭ እንዳይሆን እንደማህበር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የምንችለውን ሁሉ በማድረግ ላይ ነን ይላሉ። ከአፍሪካ ሀገራት በተለይ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ታንዛኒያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሞሮኮና ኡጋንዳ በ10 ሺና በ 5 ሺ ሜትር ሩጫ ለዘመናት በዓለም አደባባይ ላይ ገነው መታየት ችለዋል። ነገርግን እነዚህ ውድድሮች ከጨዋታ ውጪ እየሆኑ መምጣታቸውን ተከትሎ የሀገራቱ አትሌቶች በዓለም መድረክ ውጤት ለማስመዝገብ ችግር ውስጥ ገብተዋል ብለዋል። የ10 ሺ እና 5ሺ ሜትር ርቀቶች ከውድድር ውጪ እየሆኑ መምጣቱ በተለይ የአገራችን አትሌቶች ተወዳድሮ ሚኒማ የሚያሟላበት ውድድር እያገኙ ባለመሆኑ ውጤት እየራቀን ነው ያለው። ከዚህ በፊት በኢንተርናሽናል ውድድር የሚካፈሉ አትሌቶች በኢትዮጵያ ሻምፒዮና ባስመዘገቡት ውጤት መሠረት ስምንት አትሌቶች ለዓለም አቀፍ ውድድር የሚመርጡት መንገድ ነበር። ነገር ግን የ10ሺ ሜትር ውድድር ቀደም ብሎ ከተለያዩ ውድድር ውጪ እንደሆነ ይታወቃል። እንዲሁም የ5ሺ ሜትር ውድድር እአአ ከ2020 በኋላ ከዳይመንድ ሊግ ለማስወጣት በሂደት ላይ ናቸው። ስለዚህ በዳይመንድ ሊግ ላይ እነዚህ ውደድሮች ካልተካሄዱ ውድድሮቹን ስፖንሰር የሚያደርጋቸው ስለሌለ በሌሎች ውድድሮች ላይ አይካሄዱም ማለት ነው። ይሄ ከሆነ ደግሞ እኛ አፍሪካውያን ውድድሮቹ ውጤት የምናስመዘግብባቸው በመሆኑ አትሌቶቻችን ከውድድር ውጪ እየሆኑ ይመጣሉ። የአፍሪካ መለያ የሆኑት የ5 ሺ እና የ10 ሺ ሜትር የረጅም ርቀት ውድድሮች ከዓለም የውድድር መድረኮች መሰረዛቸው በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ክለቦች በረጅም ርቀት ስፖርት ታቅፈው በሥልጠና ላይ ያሉ አትሌቶች ክለቦች ሊያሰናብቱ ወይም ሊበትኑን ይቸላሉ የሚል ስጋት ተጋርጦባቸዋል ብለዋል። ነጮች በነዚህ ውድድሮች አፍሪካውያንን መቋቋም ስላልቻሉ ቀስበቀስ ስፖርቱን ከተሳትፎ ውጭ እያደረጉ ይገኛሉ ያሉት ኮማንደሩ፤ ጥቁሮች በረጅም ርቀት ውድድሮች ከመንገሳቸው በፊት አውሮፓውያን በርቀቱ ነግሰው እንደነበር ታሪክ ያስረዳል። ነገርግን ጥቁር አፍሪካውያን በተለይ ምሥራቅ አፍሪካዎች ጠንክረው በመስራት እነዚህን ውድድሮች የግላቸው ለማድረግ ችለዋል። ምሥራቅ አፍሪካውያንም ለዘመናት በመፈራረቅ በነዚህ ውድድሮች ገድል መስራት ችለዋል። ስለዚህ የአገራችንና የሌሎች አፍሪካውያን አትሌቶች ከዚህ ታሪክ በመነሳት ነጮች የአጭር ርቀት ሩጫ የግላችን ነው ብለው የሚኩራሩበትን ታሪክ ለመቀየር ጠንክሮ በመስራት በነዚህ ርቀቶች ላይ ዳግም በመንገስ ብቃታቸውን ሊያስመሰክሩ ይገባል። ኮማንደሩ አክለውም፤ የአጭር ርቀት ሩጫ ስልት የሚጠይቅ፣ የተለያዩ መሠረተ ልማቶችና ቁሳቁሶች የሚያስፈልጉት እንደሆነ ይታወቃል፤ ሌሎች አፍሪካውያን ሀገሮች ችግሩን ቀድመው በመረዳት በአጭር ርቀት ሩጫ ተተኪና ተወዳዳሪ አትሌቶችን ለማፍራት ወደታች ወርደው ግንዛቤን በመፍጠር በአጭር ርቀት ሩጫ ላይ ጠንክረው በመስራት በዓለም መድረክ ውጤት እያስመዘገቡ ይገኛሉ። ለአብነትም የአትሌቲክስ ስፖርት ተቀናቃኞችን ጎረቤታችን ኬንያን ብናይ፤ የረጅም ርቀት ሩጫዎች ከውድድር ውጪ እየወጣ መሆኑንና በአጭር ርቀት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት ወደታች ወርደው ግንዛቤውን በመፍጠርና ጠንክረው በመስራት በዓለም መድረክ በተካሄዱ የአጭር ርቀት ውድድሮች ላይ በመሳተፍ፤ በ3ሺ ሜትርና በሌሎች የአጭር ርቀት ውድድሮች የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ መግባት እየቻሉ ነው። በተጨማሪም ደቡብ አፍሪካ ናይጀሪያ ሞሮኮ የመሳሰሉ የአፍሪካ ሀገራት የኬንያን ፈለግ በመከተል በአጭር ርቀት ሩጫዎች ላይ ጠንክረው በመስራት ላይ ሲሆኑ፤ ጥሩ ውጤት እያስመዘገቡ መጥተዋል። አገራችን የሌሎች አፍሪካ ሀገሮችን ፈለግ በመከተልና በአጭር ርቀት የተሻለ ውጤትና ልምድ ያላቸውን ሀገሮች አሠራር በመቅሰም፤ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ፣ የስፖርት ማህበረሰቡና የሚመለከታቸው አካላት አንድ ላይ በመሆን ወደታች ወርደው በክልል፣ በዞን፣ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ ለአትሌቶች ግንዛቤውን በመፍጠር ስፖርተኞች በአጭር ርቀት እንዲፈጠሩ የማድረግ ሥራ መስራት እንዳለባቸው ኮማንደሩ አሳስበዋል። በአትሌቲክሱ\nስናስመዘግብ\nየቆየነው\nውጤት ተጠብቆ እንዲቀጥል በመላ አገሪቱ በአጭር ርቀትና በሌሎች ዘርፎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ለአጭር ርቀት ሩጫ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይኖርበታል። ነገር ግን ርቀቱ አቅምና ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ስልትና ብዙ ድጋፍ የሚያስፈልገው በመሆኑ፤ ፌዴሬሽኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በስፖርቱ ውጤት እንዲመጣ ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል። በአጠቃላይ ሀገራችን የምትታወቅበት የረጅም ርቀት ሩጫዎች ከውድድር ውጪ እየሆኑ መምጣታቸውን ለአትሌቶችና ለስፖርት ማህበረሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ መስራት ያስፈልጋል። ስለዚህ ግንዛቤውን በመፍጠር በርቀቱ ላይ በስፋት ጠንክሮ በመስራት ተተኪና በዓለም መድረክ ተወዳዳሪ የሆኑ ስፖርተኞችን እንደ ሀገር ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል ኮማንደሩ። ኢትዮጵያ ልክ እንደ ማራቶን፣ ግማሽ ማራቶን፣ 10ሺ፣ 5ሺ የመሳሰሉ የስፖርት ዓይነቶች ላይ ጠንከር ያለ ሥልጠናዎች በማድረግና ከታች ጀምሮ ተተኪ ስፖርተኞችን በማፍራት በኩል ያላትን ልምድ በመጠቀም በአጭር ርቀት ሩጫም ጠንክራ ሥራን መስራትና እንደ ሌሎች የአፍሪካ አገራት ውጤት ማምጣት ያለባት በመሆኑ አትሌቶች ወደ አጭር ርቀት ሩጫ በመምጣት ውጤት ለማስመዝገብ መስራት ያለባቸው አሁን ነው። በተጨማሪም 10ሺ እና\n5ሺ ሜትር ሩጫዎች የባህል ስፖርቶቻችን ናቸው ያሉት ኮማንደሩ፤ ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ አትሌት በምን ውድድር መሳተፍ ትወዳለህ ቢባል በ5ሺ\nወይም በ10ሺ ሜትር\nሩጫዎች ነው የሚለው። ምክንያቱም ከጥንት ጀምሮ ብርቅዬ አትሌቶቻችን በዓለም መድረክ በነዚህ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ታሪክ በመስራት የሀገራቸውን ሰንደቅ አላማ ከፍ አድርገው ማውለብለብ ስለቻሉ። ስለዚህ የመገናኛ\nብዙኃን የስፖርት ቤተሰቡ\nበአጠቃላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ\nከአትሌቶቹና ከፌዴሬሸኑ ጎን በመሆን\nየአገሪቱ የአትሌቲክስ ስፖርት\nእንዲያድግ መታገል አለበት።\nእንዲሁም የ5ሺ ሜትር\nሩጫ በመጪው ዓመት\nከዳይመንድ ሊግ እንዳይወጣ\nለአንድ ተቋም ብቻ የምንሰጠው\nጉዳይ ስላልሆነ ተቃውሞአችን\nለዓለም እንዲሰማ ሁሉም\nባለድርሻ አካላት በተባበረ\nክንድ የበኩሉን እንዲወጣ\nኮማንደሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 4/2011በሶሎሞን በየነ ", "passage_id": "3b22faa53c14ac23a31d3ed39c507e9b" } ]
77c62b39a4ed1398813f149cfd92c6b4
31e5bf9ac963fa6c7f5c24fc32d4c389
በክልሉ ያለውን ሰፊ የቱሪዝም ሀብት አልምቶ ጥቅም ላይ ማዋል ላይ ክፍተቶች መኖራቸው ተነገረ
 ሃይማኖት ከበደ አዲስ አበባ፡- በኦሮሚያ ክልል ሰፊ የቱሪዝም ሀብት ቢኖርም ሃብቱን አልምቶ በጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ክፍተቶች እንዳለበት የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ሁንዴ ከበደ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ በክልሉ በርካታ የቱሪስት መስህቦች ቢኖሩም ያለውን ሀብት በሚፈለገው ልክ አልምቶ ለቱሪስቶች ምቹ ሆኖ እንዲጎበኝና ጥቅም ላይ እንዲውል አልተደረገም። ለዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ ያለመሰራቱም በክልሉ ያለውን የቱሪስት ፍሰት አነስተኛ አድርጎታል። እንደ አቶ ሁንዴ ገለጻ፤ ለዘርፉ ከተሰጠው አናሳ ትኩረት ባለፈ ለክልሉ የቱሪስት ፍሰት አነስተኛ መሆን ምክንያት የሆኑት ነገሮች መካከል የሰላምና የፀጥታ ጉዳይ፣ በየደረጃው ያላው ግንዛቤ አናሳ መሆን፣ በዘርፉ ዕውቀትና ክህሎት ያለው የሰው ሀይል እጥረት፣ የመሰረተ ልማት ችግሮችና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው። በክልሉ በአመት ውስጥ በሚከበሩበት በሃይማኖታዊ ክብረ በዓላት፣ለኢሬቻ፣ ለድሬ ሼክ ሁሴንና የመሳሰሉት በዓላት ምክንያት የሀገር ውስጥ ቱሪስት ፍሰቱ ከፍተኛ ቢሆንም የውጪ ሀገር ቱሪስት ግን ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል ምክትል ቢሮ ኃላፊው። ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ ያለ ዘርፍ ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ የቱሪዝም ስራ ብዙ ወጪ የሚጠይቅ ስራ በመሆኑና ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር ዘርፍ ስለሆነ መንግስትም ከዚህ በበለጠ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራበት እንደሚገባ ገልጸዋል። አሁን ላይ በክልሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በመለየት የቱሪዝም ፍኖተካርታ ተዘጋጅቶ በመሰራት ላይ መሆኑን በመጠቆምም፤ ያለው የቱሪዝም ሀብት ለምቶና ተዋውቆ ጎብኚን እንዲስብ የተለያዩ የማስተዋወቂያ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ አቶ ሁንዴ ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ቱሪስት እንዲመጣ የሚያደርጉት በአብዛኛው አስጎብኚ ድርጅቶች ናቸው፤ በሀገሪቱም በርካታ የአስጎብኚ ድርጅቶች ቢኖሩም የክልሉን ሀብት ፓኬጅ ውስጥ አስገብቶ መስራት ላይ ክፍተት አለ። ከቱሪስት ፍሰቱ ጋር ተያይዞ በክልሉ ትልቅ ችግር የሚነሳው ከልማት ጋር ተያይዞ ያለው ነገር ሲሆን፤ ቱሪስቶች ወደ ክልሉ ሲመጡ በቂ የሆነ የሚያድሩበትና የሚመገቡበት ስፍራ አለመኖሩ አንዱ ችግር ነው። ለአብነትም፣ በባሌ አካባቢ የተለያዩ ለዩኔስኮ የታጩ ቦታዎች ቢኖሩም፤ ወደ እዛ ሲኬድ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሉም። ስለዚህ ቱሪስት ቢሄድም የሚያድርበት የሚዝናናበት ቦታ ስለሌለ ይሄ ነገር እንደ ስጋት ይታያል። ከዚህ አንፃር በክልሉ በቀጣይ አስር ዓመታት ወደ 25 የሚሆኑ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎች እንዲለሙ በዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል። በተለይ የመሰረተ ልማት ስራዎች ቅድሚያ ተሠጥቷቸው እንዲሰሩ ቢሮ ትኩት አድርጎ እየሰራ መሆኑን እና ከመንግስትና ከግል ባለሀብቱ ጋር በጋራ በመሆን ቱሪስቶች ሊጠቀሙባቸው ነገሮችን ለማሟላት እየተሰራ ነው ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37934
[ { "passage": "በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዝናቡ ቱኑ ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ሀብቱ ከሸሸባቸው አገራት ጋር የተደረገው ውይይት ሁሉም አገራት በሚባልበት ደረጃ ሰምምነት ላይ መደረሱን ጠቅሰው በወንጀል የተገኘ ሀብት የማስመለስ ዳይሬክቶሬት መቋቋሙንም ተናግረዋል።\n\nከአገራቱ ጋር ባለው ንግግር የተዘረፈው ሀብት በምን መልኩ ይመለሳል? የሚለውን ለመወሰን ያሉ ዓለም አቀፍ ሕግጋትን እያጠኑ እንደሆነና በድርጊቱ ውስጥ የተሳተፉ አካላት በምን አግባብ እንደሚጠየቁ እየተሰራበት እንደሆነም ለቢቢሲ አስረድተዋል። \n\n• ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ኢትዮጵያ ውስጥ ደብዛው የጠፋው ኤርትራዊ ምርመራ እንዲጠናቀቅ መመሪያ ሰጠ\n\n• በተሻሻለው የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ህግ ረቂቅ ጥፋተኛና አቃቤ ህግ ይደራደራሉ \n\n• የሐኪሞች እጅ ጽሑፍ የማይነበበው ለምንድን ነው?\n\nገንዘቡ ወዴት ሀገር ሸሸ? ምን ያህል ገንዘብ ከአገር ወጥቷል? የሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ አግኝተዋል የሚሉት አቶ ዝናቡ፤ ምን ያህል የገንዘብ መጠን ወደ የትኞቹ አገራት ሸሽቷል? የሚለውን \"እየተሰራ ያለውን ሥራ ያደናቅፋል\" በሚል ከመግለጽ ተቆጥበዋል። \n\nአቶ ዝናቡ ቱኑ በዚህ ወንጀል የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን ለሕግ የማቅረብ፣ ገንዘቡን የማስመለስ ዝርዝር መረጃዎችን ጊዜው ሲደርስ ይገለፃል በማለት ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።\n\n\"አሁን ባለው መረጃ ሀብቶቹን የማሸሽ ተግባራት ላይ ተሳትፈው የነበሩት የመንግሥት መዋቅር ውስጥ የነበሩና ተባባሪዎቻቸው ናቸው\" ያሉት አቶ ዝናቡ፣ \"ሀብቱን የመዘበሩ አካላት ለሕግ መቅረባቸው አይቀሬ ነው\" ብለዋል።\n\nአቶ ዝናቡ እነዚህን ግለሰቦች በሕግ ፊት አቅርቦ ለመጠየቅ የሚያስችል ጥናት እየተካሄደና ማስረጃ ተሰባስቦ እየተደራጀ መሆኑንም ጨምረው በመግለጽ \"ማንም በዚህ ወንጀል የተሳተፈ ሳይጠየቅ አይቀርም\" ብለዋል።\n\nይህ ሥራ ከዚህ በፊት ተጀምሮ ቢቆይም በልምድ ማነስ ምክንያት የሚፈለገውን ውጤት አለመምጣቱን በመግለጽም አሁን ግን ሀብት የማስመለስ ስትራቴጂ መቀረጹን ገልፀዋል። ይህንን ሊመራ የሚችል የሥራ ክፍል መዋቀሩንም ኃላፊው ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።\n\nሀብት ማሸሽ በርካታ መልኮች እንዳሉት የጠቀሱት አቶ ዝናቡ \"ከአገር የወጣ ሀብት በተለያየ መልኩ ለወንጀል ተግባራት ውሏል፣ በሕገ ወጥ መንገድ የወጣ ሀብትን መልሶ ሕጋዊ በማስመሰል የመጠቀም አዝማሚያ ነበር\" ብለዋል።\n\nመንግሥት ከገንዘብ ዝውውርና መሰል ተግባራት ጋር ከሚሰሩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመስራቱ የኢትዮጵያ ስም ከእነዚህ አገራት ተርታ እንዲሰረዝ ማድረጉንም አቶ ዝናቡ ተናግረዋል።\n\n\"ፋይናንሻል አክሽን ታክስ ፎርስ\" የተባለው ተቋም ኢትዮጵያ ሀብት ከሚሸሽባቸው አገራት ዝርዝር ውስጥ ለመውጣት እየሰራችው ያለው ሥራ የሚያስመሰግን ነው በሚል ስሟን ሀብት ከሚሸሽባቸው አገራት መካከል እንድትወጣ መደረጉን ገልጸዋል። \n\n ", "passage_id": "b635b7658ed223a952025ba038edf08c" }, { "passage": "በ2007/08 ዓ.ም የፌዴራል ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከዓለም ቱሪዝም ድርጅት ጋር በመቀናጀት አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች ክልል ከተሞች የሆቴሎች የኮከብ ደረጃ ምደባ መስጠት መጀመሩ ይታወሳል፡፡ ለ54 ሆቴል የኮከብ ምደባ ተደርጎላቸውም ነበር፡፡ ከዚያ በኋላም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁለት ዙር የሆቴል ደረጃ ምደባ ተከናውኗል፡፡በሆቴሎች ከመኝታ ክፍል ጀምሮ በተለያዩ ክፍሎች ከሚሰጡት አገልግሎቶች፣ የግቢ ገጽታ፣ የቀለም፣ የጽዳትና ውበት፣ የመጠን፣ የርዝመት፣ የወርድና ሌሎችም መመዘኛ መስፈርቶች ታይተው ደረጃው እንደሚሰጥ ከአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የቱሪስት አገልግሎት ብቃት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡የኮከብ ደረጃም ሲሰጥ በአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናና ጥራት ልዩነት እንደሚኖር ተጠቅሷል፡፡ ለአብነት ባለአንድና ባለሁለት ኮከብ ሆቴል መዋኛ ገንዳ እንዲኖራቸው አይገደዱም፤ በአንጻሩ ኮከብ አራትና አምስት የተሰጣቸው መዋኛ ገንዳ እንዲኖራቸው ይፈለጋል፡፡ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ቱሪስት አገልግሎቶች ብቃት ማረጋገጥና ደረጃ ምደባ ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ደግሞ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከያና መቆጣጠሪያ ዘዴዎች፣ ጽዳትና የንጽሕና አጠባበቅ ሥርዓትና ሌሎች መስፈርቶች ይሟሉ እንጂ አንድ ወይም ሁለት መዝናኛ ስፍራ አለመኖራቸው ለኮከብ ደረጃው ማግኘት የነበረባቸውን ነጥብ እንዳያገኙ ብቻ የማድረግ ተፅዕኖ እንዳለው አመላክቷል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሆቴል አብዛኛውን መመዘኛ መስፈርቶች አሟልቶ መዋኛ ገንዳ ስለሌለው ብቻ የአራተኛ ወይም አምስተኛ ኮከብ ደረጃውን ሊከለከል እንደማይችል መረጃው ያሳያል፡፡ከዚህ አኳያ ሲቃኝ በአማራ ክልል የሆቴል አገልግሎት በዕውቀትና መርህ ላይ ተመሥርተው እየተከፈቱ እንዳልሆነ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ቱሪስት አገልግሎት ብቃት ማረጋገጥ ዳይሬክተር አበራ ባልዳ ገልጸዋል፡፡ አብዛኛው ባለሀብት ገንዘብ ስላለው ብቻ ሆቴል መክፈት እንደሚፈልግም ጠቁመዋል፡፡መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች፣ ቦታ፣ ሙያዊ ድጋፍና የማማከር ሥራ ሳይከናወን ወደ ግንባታ እንደሚገባም ነው የገለጹት፡፡ የሆቴል ግንባታ ሥራውን (ፕሮጀክቱን) ፈቃድ የሚሰጠውና የሚቀበለው ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ነው፡፡ በዚህም ተቀናጅተው እየሠሩ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሆቴል መገንባት እንፈልጋለን የሚለው ጥያቄ ከባለሀብቶች ሲቀርብለት ወደ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ መላክ እንዳለበትም ጠቅሰዋል፤ ነገር ግን ተግባቦቱና መናበቡ ድክመት እንዳለበት አመላክተዋል፡፡ የስምምነት ፊርማ ተካሂዶም ለውጥ አልታየበትም ይላሉ፡፡በዚህ ወቅት የሆቴል ማስፋፊያ እንዲፈቀድ የድጋፍ ደብዳቤ ጥያቄ ጋጋታ መኖሩን አንስተው አስቀድሞ ግን ደረጃቸውን በጠበቀ ሁኔታ ቢገነቡ እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮች እንደማይከሰቱ አስረድተዋል፡፡ በውጤቱም በደረጃ ምዘናው 50 ከመቶ ሆቴል ኮከብ ውስጥ እየገባ እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡ ከንድፍ ጀምሮ ስህተቶች ስለሚሠሩ ግንባታው ተጠናቅቆ ወደ አገልግሎት ከገቡ በኋላ ለማስተካከል አዳጋች እንደሚያደርገው አንስተዋል፡፡ባሉት ግብዓቶች ለማስተካከል ሲሞከርም ባለሀብቶች ወጪ ላለማውጣት የፈቃደኝነት ችግር እንደሚስተዋልባቸው ተናግረዋል፡፡ በሁለት ዙር በተካሄደው ምዘና በክልሉ 32 ሆቴል ከአንድ እስከ አራት ኮከብ ደረጃ ውስጥ ገብተዋል፡፡ለቱሪዝም ነክ መስኮች ፈቃድ ሲሰጥ ለሚገነባበት ስፍራ ተቋማት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርጉ ደብዳቤ እንደሚጻፍ የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ባለሙያ ታደሰ በላይ አመላክተዋል፡፡ ከሚመለከተው የከተማም ይሁን የወረዳ መዋቅር የባህልና ቱሪዝም ቢሮ መረጃዎችን መውሰድ እንደሚችልም አቶ ታደሰ ተናግረዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጸደቀው ዓዋጅ መሠረት ፈቃድ ከመሰጠቱ በፊት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ዕውቅና ይኑረው የሚል ቅድመ ሁኔታ አለመቀመጡንም ጠቅሰዋል፡፡ ይህም የአሠራር ችግር እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡ወደፊት ግን ፈቃድ ከመሰጠቱ በፊት የሚለው አካሄድ በኃላፊዎች ደረጃ ከታመነበት መተግበር እንደሚችልና ዓዋጁ ግን እንደማያዝዝ ገልጸዋል፡፡ መረጃ የማይደርስ ከሆነ የታችኛውን መዋቅር ማስተካከል አንድ የመፍትሔ ሐሳብ መሆኑንም ባለሙያው አንስተዋል፡፡", "passage_id": "86b28dc1b9b3cad53825fad38bd7cf58" }, { "passage": "የኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በኢትዮጽያ የሚገኙ የተለያዩ የማይዳሰሱና የሚዳሰሱ ቅርሶችን ለአለም ለማስተዋወቅ እየሰራ ይገኛል፡፡በየአመቱ መስከረም 17 በሚከበረው የአለም የቱሪዝም ቀንን በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች በማክበር ኢትዮጽያን በቱሪዝም ዘርፍ ባላት ሀብት ቀዳሚ ለማድረግ የሚያደርገው እንቅስቃሴ አንዱ ነው፡፡የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎች አለመኖርና የበጀት እጥረት እንዳለበትም የሚኒስቴሩ የህዝብና አለምአቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ገዛከኝ አባተ ከዋልታ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል፡፡ከባለሙያ አለመኖር ጋር ተያይዞ ከውጭ ሀገራት ባለሙያ በማስመጣት የሚደረገው የጥገና ስራ ለዘርፉ ከሚውለው  ከፍተኛ በጀት እንደሚወስድ የሚታይ እውነታ እንደሆነም ዳይሬክተሩ አስረድተዋል ።በዚህም ምክንያት ስጋት ላይ የሚገኙትን ቅርሶቻችንን በሙሉ ጥገና ማከናወን አልቻልንም ሲሉ ገልጸዋል፡፡የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴርና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን በቅርስ ጥገናና ጥበቃ ዙሪያ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል ምክክር መደረጉንም ገልጸዋል፡፡ሁሉም ዜጋ በሀገሪቱ ያሉ ቅርሶችን የመጠበቅ ሀላፊነት አለበትና በዘርፉ ለመሰማራት ለሚፈልግ ማንኛውንም ዜጋ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በር ክፍት ነውም ብለዋል፡፡", "passage_id": "df17ce0984b288db9324d2936beeff0c" }, { "passage": "የኢትዮጵያን  የቱሪዝም እምቅ አቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ 5ነጥብ5 ሚሊዮን ብር መመደቡን የኢትዮጵያ ቱሪዝም ደርጅት አስታወቀ ።የድርጅቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጀማነህ ከድር እንደገለጹት ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ተደራሽነት  ባላቸው  መገናኛ ብዙሃን የማስተዋወቅ ሥራ  ለማከናወን ነው  የተመደበው   በጀት  የሚውለው ።አዲሱን የቱሪዝም መለያ የአማርኛ አቻ ትርጓሜ \"ምድረ-ቀደምት\" ደግሞ ለአገር ውስጥ ቱሪስቶች እናስተዋውቃለን\" ብለዋል።ኢትዮጵያ ያላትን የቱሪዝም አቅም ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብና ለአገር ውስጥ ጎብኚዎች የማስተዋወቁ ስራ በቀሪው ሩብ ዓመት እንደሚከናወንም ነው የተናገሩት።የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላትም ቱሪዝሙን በማስተዋወቅ የአገሪቷን መልካም ገጽታ ለመገንባት የድርሻቸውን እንደሚወጡ  ይደረጋል ብለዋል አቶ ጀማል ።( ኢዜአ) ", "passage_id": "cb19fc3628008be4960b1f24d25609fb" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው ፡፡በጉባኤው ላይ በቱሪዝም ዘርፍ ላይ በየጊዜው የሚነሱ ተመሳሳይ ችግሮችን ለመፍታት አሁንም ከፍተኛ ትኩረትና የቅንጅት ስራ እንደሚያስፈልግ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ወልደማርያም አስታውቀዋል፡፡በጉባኤው እየተደረገ ባለው ውይይት ዘርፉን ለማዘመን ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም አንጻር አሁንም ሰፊ ስራዎች እንደሚቀሩ ተመልክቷል፡፡ከፓርኮች ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ የሚነሱት ችግሮች እየተፈቱ አለመሆኑ እና ከቅርሶች እድሳት ጋር በተያያዘ ደግሞ የነባር ይዞታዎች መጥፋት ችግሮች መኖራቸው እንዲሁም በዘርፉ አሉ ተባሉ ሌሎች ችግሮች በምክር ቤቱ አባላት ተነስተዋል።ለጥያቄዎቹም የምክር ቤቱ የቦርድ ሰብሳቢ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ምላሽና አቅጣጫዎች ይሰጡበታል ተብሎ ይጠበቃል-(ኤፍ ቢ ሲ) ፡፡", "passage_id": "fdbf974efb1acc571db192b87fc18aee" } ]
2f2cbf4dddbc7b4082297bc69c93ca50
30bda8c63d28386ab69be25196b788c0
ሰባት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ፍርድ ቤት ቀረቡ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- እነ ሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፍቃዴን ጨምሮ 7 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። ኢቢሲ እንደዘገበው፤ በሀገር ክህደት ወንጀል የተጠረጠሩት የመከላከያ የመገናኛ ሬዲዮ መምሪያ ኃላፊ የነበሩት እነ ሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፍቃዴን ጨምሮ 7 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ትናንት ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድን ተጠርጣሪዎች ላይ ከዚህ ቀደም ሲያቀርብ ከነበረው የወንጀል ተግባራት ባሻገር “በርካታ የመገናኛ ሬዲዮ ይወገድ በሚል ምክንያት ከማዕከል አጓጉዘው ለትግራይ ልዩ ኃይል ስለማስረከባቸው ያገኘሁት ማስረጃ ያመላክታል” ብሏል። የምርመራ ቡድኑ ተጠርጣሪዎች የሰሜን ዕዝ መገናኛ ሬዲዮ እንዲቋረጥ ትዕዛዝ ሰጥተዋልም ብሏል፤ ሌሎችንም በመጥቀስ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀን ጠይቋል። የተጠርጣሪ ጠበቆች የደንበኞች የወንጀል ተሳትፎ ተለይቶ አልቀረበም፣ ተጨማሪ ጊዜ ለምርመራ ቡድኑ መፈቀድ የለበትም ብሏል። ችሎቱ ትዕዛዝ ለመስጠት ለታኅሣሥ 15 ቀን 2013 ቀጥሯል።በተያያዘ ዜና፣ ከመከላከያ ሰራዊት በጡረታ የተገለሉ አባላትን በማሰባሰብና በመመልመል የትግራይ ልዩ ሃይልን እንዲቀላቀሉ ሲያደርጉ ነበር የተባሉ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ዘግቧል። በዘገባው እንደተመላከተው፤ ከአራቱ መካከል ከኮሎኔል ገብረመድህን ገብረመስቀል በስተቀር ቀሪዎቹ ከሰባት አመት በፊት በጡረታ የተገለሉ ሲሆኑ፤ ተጠርጣሪዎቹ ህገ መንግስቱን እና ህገ መንግስታዊ ስርአቱን በሃይል በመናድ ወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ እየተከናወነባቸው ይገኛል። እነዚህም 1ኛ ኮሎኔል ምሩፅ በርሄ፣ 2ኛ ኮሎኔል ገብረመድህን ገብረመስቀል፣ 3ኛ ኮሎኔል ተስፋዬ ሃጎስ እና 4ኛ ኮሎኔል መብራቱ ተድላ ናቸው። መርማሪ ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው 12 ቀናት ውስጥ የሰራቸውን በርካታ የምርመራ ስራዎች ለችሎቱ አብራርቷል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ከሜጄር ጄኔራል ገብረመድህን ፍቃዴ (ወዲ ነጮ) ጋር በመሆን በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ኔትወርክ ግንኙነትን በማቋረጥ ተሳትፎ እንዳላቸው በሰው ምስክርና በቴክኒክ ምርመራ በማስረጃ አረጋግጫለሁ ብሏል። የስምንት ሰዎችን የምስክርነት ቃል መቀበሉን የገለጸው መርማሪ ፖሊስ፤ በትግራይ ክልል የፌደራል ፖሊስ አባላትና ተቋማት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ለይቶ በማስረጃ በማረጋገጥ ከመዝገቡ ጋር ማያያዙንም ጠቅሷል። ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ከወንጀሉ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው በመጥቀስ የወንጀል ተሳትፏቸው ተለይቶ አለመቅረቡን በማንሳት በነጻ አልያም በዋስ እንዲወጡ ጠይቀዋል። መርማሪ ፖሊስም የእያንዳንዳቸውን ተሳትፎ ያብራራ ሲሆን በዚህም 1ኛ ተጠርጣሪ በሚሰሩበት የጥበቃ ስራ ላይ የራሳቸውን አባላት መልምለው በፌደራል ተቋማት ላይ ጥቃት ሊፈጽሙ እንደነበር በሰበሰብኩት ማስረጃ አረጋግጫለሁ ነው ያለው። እንዲሁም 2ኛ ተጠርጣሪ ሁለት ጊዜ በተሰማሩበት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ አባላትን አደራጅተው የትግራይ ልዩ ሃይልንእንዲቀላቀሉ ማድረጋቸውን ማስረጃ መሰብሰቡን ጠቅሶ፤ 3ኛ ተጠርጣሪም ወንጀሉ ሲፈጸም ህክምና ላይ ነበሩ ተብሎ በጠበቃቸው ለተነሳው መቃወሚያ መርማሪ ፖሊስ ወንጀሉ ሲፈጸም ብቻ ሳይሆን ለወንጀሉ መፈጸም ከሁለት አመት በፊት ጀምሮ ለፀረ ሰላም ቡድኖች መረጃ ሲያቀብሉ እንደነበርም ማስረጃ መሰብሰቡን አስረድቷል። 4ኛ ተጠርጣሪም ቢሆኑ ከሜጀር ጀኔራል ገብረመድህን ጋር በመገናኘት ከመከላከያ በጡረታ የወጡ ሰዎችን በመሰብሰብ ለትግራይ ልዩ ሃይል አባላትን ሲመለምሉ እንደነበር ማስረጃ መሰብሰቡንም ነው ያስረዳው። ከዚህ ባለፈም በአዲስ አበባ ከተማ እያንዳንዳቸው ያደርጉት የነበረውን እንቅስቃሴ ማጣራቱንም ጠቅሷል። የሁለቱን ክርክር ያዳመጠው ችሎቱ ተጠርጣሪዎቹ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት እንዳላቸው ጠቅሶ መርማሪ ፖሊስ ምርመራውን በፍጥነት እንዲያከናውን ትዕዛዝ ሰጥቷል። ለተጨማሪ ምርመራም ለፖሊስ 10 ቀናትን ፈቅዷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37931
[ { "passage": "በተለያዩ የፌዴራል ተቋማት ላይ ለጥበቃ ሥራ የተሰማሩ ግለሰቦችን በመመልመል በፌዴራል ተቋማት ላይ ጥቃት እንዲያደርሱና ከመከላከያ ሠራዊት በጡረታ የተሰናበቱ ወታደሮችን በማሰባሰብ፣ የትግራይ ልዩ ኃይልን እንዲቀላቀሉ በማድረግ የተጠረጠሩ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተጠየቀባቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ በማሰብ፣ እንዲሁም የሰሜን ዕዝ የመከላከያ ግንኙነት በማቋረጥ የመከላከያ ሠራዊቱ ጥቃት እንዲደርስበት በማድረግ ተጠርጥረው በእስር ላይ ከሚገኙት እነ ሜጀር ጄኔራል ገብረ መድኅን ፍቃዴ (ወዲ ነጮ) ጋር በመገናኘት ሲንቀሳቀሱ እንደነበር፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ለፍርድ ቤት አስረድቷል፡፡ ቡድኑ ታኅሳስ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ለፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት እንዳስረዳው ተጠርጣሪዎቹ ኮሎኔል ምሩፅ በርሄ፣ ኮሎኔል ገብረ መድኅን ገብረ መስቀል፣ ኮሎኔል ተስፋዬ ሐጎስና ኮሎኔል መብራቱ ተድላ ናቸው፡፡መርማሪ ቡድኑ ቀደም ብሎ በተሰጠው 12 የምርመራ ቀናት የሠራውን ለፍርድ ቤቱ እንደገለጸው፣ የስምንት ሰዎችን ቃል ተቀብሏል፡፡ በትግራይ ክልል በፌዴራል ፖሊስ ተቋምና አባላት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ለይቶ በማስረጃ ማረጋገጡንና ከምርመራ መዝገቡ ጋር ማያያዙን ተናግሯል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ የተጠረጠሩበት የወንጀል ተሳትፎ ሰፊ ከመሆኑ አንፃር፣ ቀሪ ምስክሮችን ቃል መቀበል የሰነድ ማስረጃዎችን መሰብሰብና ግብረ አበሮችን ለመያዝ ተጨማሪ 14 ቀናት እንደሚያስፈልገው ጠቁሞ እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት የመቃወሚያ ክርክር እንዳስረዱት፣ መርማሪ ቡድኑ ከገለጸው የወንጀል ድርጊት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የላቸውም፡፡ የወንጀል ተሳትፎ አለባቸው ቢባል እንኳን ማን ምን ዓይነት ወንጀል እንደፈጸመ መርማሪ ቡድኑ ለይቶ ያቀረበው ነገር እንደሌለ በማስረዳት፣ ፍርድ ቤቱ በነፃ እንዲያሰናብታቸው ወይም የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡የተጠርጣሪዎቹን መቃወሚያና የዋስትና ጥያቄ በመቃወም የተከራከረው መርማሪ ቡድኑ በድጋሚ እንዳስረዳው፣ ኮሎኔል ምሩፅ በሚሠሩበት የጥበቃ የሥራ ቦታ አባላትን በመመልመል በፌዴራል ተቋማት ላይ ጥቃት እንዲያደርሱ ሲያዘጋጁ እንደነበር፣ ኮሎኔል ገብረ መድኅን ደግሞ በተሰማሩበት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ አባላትን አደራጅተው የትግራይ ልዩ ኃይልን እንዲቀላቀሉ ማድረጋቸውን አስረድቷል፡፡ኮሎኔል ተስፋዬ ምንም እንኳን ወንጀሉ ሲፈጸም ሕክምና ላይ እንደነበሩ በጠበቃቸው የተገለጸ ቢሆንም፣ የተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት በቅርቡ በተፈጸመ ወንጀል ብቻ ሳይሆን ከሁለት ዓመታት በፊት ጀምሮ ለፀረ ሰላም ቡድኖች መረጃ ከማቀበል ጋር በተያያዘ መሆኑን እንደነበር መርማሪ ቡድኑ አስረድቷል፡፡ኮሎኔል መብራሃቱ ደግሞ ጡረታ የወጡ የመከላከያ ሠራዊት አባላትን በመሰብሰብ ለትግራይ ልዩ ኃይል ሲመለምሉ እንደነበር ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ሲያደርጉት የነበረውን እንቅስቃሴ እያጣራ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡በሌላ በኩል በአገር ክህደት የተጠረጠሩት የመከላከያ ሬዲዮ መገናኛ መምርያ ኃላፊ የነበሩት እነ ሜጀር ጄኔራል ገብረ መድኅን ፍቃዴ (ሰባት ተጠርጣሪዎች) ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በርካታ የሬዲዮ መገናኛዎችን ‹‹‹ይወገድ›› በማለት ከማዕከል አጓጉዘው ለትግራይ ልዩ ኃይል ማስረከባቸውን የሚያሳይ ማስረጃ ማግኘቱን ለፍርድ ቤቱ መርማሪ ቡድን አስረድቷል፡፡ ቀሪ ምርመራ እንዳለው በመግለጽም 14 ተጨማሪ ቀናት ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹም የፈጸሙት ወንጀል ተለይቶ አለመቅረቡንና ዋስትና ሊጠበቅላቸው እንደሚገባ በመግለጽ አቤቱታቸውን አሰምተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹና መርማሪ ቡድኑ ያደረጉትን ክርክር ከሰማ በኋላ፣ ተጠርጣሪዎቹ የጠየቁትን ዋስትና ውድቅ በማድረግና መርማሪ ቡድኑም ምርመራውን በፍጥነት እንዲያጠናቅቅ በመንገር፣ አሥር የምርመራ ቀናት ፈቅዶ ለታኅሳስ 23 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ሲሸሹ አፋር ላይ እንደተያዙ ለተመሳሳይ ፍርድ ቤት በመግለጽ ታኅሳስ 12 ቀን 2013 ዓ.ም. ያቀረባቸው ብርጋዴር ጄኔራል ይልማ ከበደ፣ ኮሎኔል ሐርጎት በርሄ፣ ሌተና ኮሎኔል ሙሉ ዓለሙ፣ ኮሎኔል በረከት ወልደ አብዝጊ፣ ሌተና ኮሎኔል ግደይ ገብረየሱስ፣ ሻለቃ ሓሳቡ መሐመድ፣ የመቶ አለቃ ፀሐይ ኃይሉ፣ ኮሎኔል ይርጋለም ፈቃዱና ሌተና ኮሎኔል ተወልደ ብርሃን ይባላሉ፡፡ተጠርጣሪዎቹ በሥራ ላይ እያሉ ወንጀል ለመፈጸም የሥራ ክፍፍል በማድረግ ይሠሩ እንደነበር በማስረጃ ማረጋገጡን ለችሎቱ ተናግሯል፡፡ በውጭ አገር ላሉ አካላት ሐሰተኛ መረጃ ሲያቀብሉ እንደነበርና በወቅቱም በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ችግር እንዲፈጠርና እንዲስፋፋ ሲያደርጉ እንደነበርም በምርመራ ማረጋገጡን በማስረዳት፣ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት መርማሪ ቡድኑ እንደገለጸው ሳይሆን፣ በተለያዩ ቦታዎች በሥራ ላይ ነበሩ፡፡ የወንጀል ተሳትፏቸውን በጥቅል መግለጽ ተገቢ ስላልሆነ ተሳትፏቸው ተለይቶ ሊገለጽላቸው እንደሚገባ ተናግረው፣ ከተጠቀሰባቸው የወንጀል ድርጊት ጋር ምንም የሚያገናኛቸው ነገር ባለመኖሩ በነፃ እንዲሰናበቱ፣ ወይም የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡መርማሪ ቡድኑ በድጋሚ ለፍርድ ቤቱ ኮሎኔል ይርጋምና ኮሎኔል ተወልደ ሲሸሹ አፋር ላይ እንደተያዙ አስረድቶ፣ ያልተያዙ ግብረ አበሮች ስላሏቸው በዋስ ቢወጡ ሊሸሹና ጉዳት ሊያደርሱ እንደሚችሉ በመጠቆም፣ ጥያቄያቸውን ተቃውሟል፡፡ የግራ ቀኙን ክርክር የሰማው ፍርድ ቤት የተጠርጣሪዎቹን ተሳትፎ ከምርመራ መዝገቡ ዓይቶ ትዕዛዝ ለመስጠት ለሐሙስ ታኅሳስ 15 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡      ", "passage_id": "d5463b80aa41ff57c75f20e6d64a4a2f" }, { "passage": "የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት  ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ለ61 መከላከያ ሰራዊት ጄነራል መኮንኖች ከፍተኛ ወታደራዊ ማዕረግ አለበሱ ፡፡እነዚህ ከሁለት ሳምንት በፊት ወታራዊ ማዕረጉ የተሰጣቸው መኮንኖች ማዕረጋቸውን የማልበስ ስነ ስርዓቱ የተካሄደው ትናንት ማምሻውን በብሄራዊ ቤተ መንግስት በተከናወነ ስነ ስርዓት ላይ ነው ፡፡ይህም አራት የሙሉ ጀነራልነት ፣ ሶሰት የሌተናል ጄነራልነት ፣ 14 የሜጀር ጀነራልነት እና 40 የብርጋዴር ጀነራልነት ማዕረግ የተሰጣቸው ናቸው።በዚሁ ወቅት የኢፌዴሪ ፕረዝዳንት ሙላቱ ተሾመ እንደገለጹት ፤የጦር መኮንኖቹ በወታደራዊ ግዳጅ አፈጻጸማቸው የተጣለባቸውን ከፍተኛ ኃላፊነት በብቃት የተወጡ፤ በመልካም ስነ-ምግባር፣ በአመራር ችሎታ እና ብቃታቸው ብልጫ ያላቸው ናቸው ። ", "passage_id": "68f64a1ef51ec6f4b5f5796f046a5dbf" }, { "passage": "የጭንቅላት ካንሰር እንዳለባቸው ማስረጃ ያቀረቡ ኮሎኔል ዋስትና ተፈቀደላቸውበትግራይ ክልል በምዕራባዊ ዞን በሁመራ ወረዳ በምትገኘው የማይካድራ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ነዋሪ በሆኑ በአማራ ብሔር ተወላጆችና በሰሜን ዕዝ ላይ፣ ጥቃት እንዲፈጸም በማነሳሳት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉ ወታደራዊ መኮንኖችና ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ሰኞ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ከቀረቡት ተጠርጣሪዎች መካከል፣ ታጐስ ገብረ ትንሣዔ የተባለች ተጠርጣሪ አንዷ ነች፡፡ ተጠርጣሪዋ ብሔርንና ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ በማይካድራ ከተማ የተደራጁ የሽብር ቡድን አባላት ግጭት እንዲያነሱ በመቀስቀስ፣ ጭካኔ የተሞላበት አሰቃቂ ዕርምጃ እንዲወሰድ በማድረግ በርካታ ንፁኃን ነዋሪዎች እንዲገደሉ፣ አካላቸው እንዲጎድልና ከመኖሪያ ቀዬአቸው ተፈናቅለው እንዲሰደዱ ማድረጓን፣ የወንጀል ድርጊቱን እየመረመረው የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ለፍርድ ቤቱ ገልጿል፡፡ ተጠርጣሪዋ ከማይካድራ ነዋሪዎች በተጨማሪ በሰሜን ዕዝ የአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ስታደርግ እንደነበር መርማሪ ቡድኑ አስረድቶ፣ በተፈጸመው የወንጀል ተግባር ዙሪያ ምርመራዎችን ለማድረግ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡ ፍርድ ቤቱ በዕለቱ የ31 ተጠርጣሪዎችን የምርመራ ውጤት የተመለከተ ሲሆን፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን አስቀድሞ ያቀረበው በንግድ ሥራ ላይ ተሰማርተው በትግራይ ክልል ውስጥ መሽገው ሕገወጥ ተግባር ሲፈጽሙ የነበሩ ቡድኖችን ሲረዱ ነበር ያላቸውን ነው፡፡ በዚህም መሠረት አቶ ተስፋሁነኝ ንጉሥ፣ አቶ ተስፋ ገብረ ሚካኤል፣ አቶ ቶማስ ገብረ ሚካኤል፣ አቶ መኩሪያ ኪዳኔና አቶ ብሩክ ካሳዬ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መሆናቸውን ተናግሯል፡፡ ተጠርጠሪዎቹ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ በማሰብ በትግራይ ክልል መሽገው ከነበሩ ሕገወጥ የሕወሓት ቡድን ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ በአገሪቱ ሰላምና ፀጥታ እንዳይኖር፣ ሁከት፣ ረብሻና አለመረጋጋት እንዲፈጠር በገንዘብ ሲረዱ እንደነበር መርማሪ ቡድኑ አስረድቷል፡፡መርማሪ ቡድኑ በተጠርጣሪዎቹ ላይ የበርካታ ምስክሮችን ቃል መቀበሉንና ሰፊ ምርመራ መሥራቱን ጠቁሞ፣ ቀሪ የምስክሮችን ቃል መቀበል፣ በብርበራ የተገኙ የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎች ምርመራ ውጤት መቀበል፣ ወደ ክልል ለምርመራ የተላከ የምርመራ ቡድን ውጤት መቀበል፣ ከባንክና ከተለያዩ አካሎች የሰነድ ማስረጃዎችን መሰብሰብ እንደሚቀረው በመግለጽ፣ ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ባቀረቡት ክርክር መርማሪ ቡድኑ የሚፈልገውን ማስረጃ ስላገኘ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ሊሰጠው እንደማይገባ፣ የባንክ ሒሳባቸው ስለታገደ ቤተሰቦቻቸው ችግር ላይ መሆናቸውን፣ ዕግዱ እንዲለቀቅላቸውና የዋስትና መብታቸው ተፈቅዶላቸው በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ የተጠርጣሪዎቹን አቤቱታ የተቃወመው መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ እንደገለጸው፣ የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ከደቡብ ቴፒ እስከ ሰሜን ጎንደርና ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ እስከ አፋር ድረስ በመሆኑ ውስብስብ፣ አገርን ከሚያተራምሱ የሕወሓትና የኦነግ ሸኔ ቡድን አባላት ጋር በኔትወርክ የሚገናኙ በመሆናቸው፣ ድርጊቱ ሰፊ ምርመራ የሚያስፈልገው መሆኑን አስረድቷል፡፡ ተጠርጠሪዎቹ በርካታ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲገደሉ በማድረጋቸው ተጠርጥረው በመፈለግ ላይ ያሉት የእነ ጽብረ ጺዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) እና የእነ አቶ ጌታቸው አሰፋ ግብረ አበሮች መሆናቸውን በማስረዳት፣ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ በሌላ መዝገብ የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ደግሞ ብርጋዴር ጄኔራል ምሩፅ በርሄ (በኮሮና በመያዛቸው አልቀረቡም)፣ ኮሎኔል ገብረ መድኅን ገብረ መስቀል፣ ኮሎኔል ተስፋዬ ሐጐስና ኮሎኔል መብራቱ ታደሰ ሲሆኑ፣ እነሱም ከላይ እንደተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር መርማሪ ቡድን ገልጿል፡፡ የምስክሮችን ቃል መቀበሉን፣ የተጎጂ ሰዎችን ሁኔታ በማጣራት ላይ መሆኑንና ቀሪ ሰፊ ምርመራና የምስክሮች ቃል መቀበል እንደሚቀረው በማስረዳት ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹም ለመርማሪ ቡድኑ ተጨማሪ ጊዜ ሊፈቀድለት እንደማይገባ በመቃወም፣ የዋስትና መብታቸው ተከብሮላቸው በውጭ ሆነው እንዲከራከሩ እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡ ኮሎኔል ተስፋዬ ሐጐስ የተባሉት ተጠርጣሪ የጭንቅላት ካንሰር እንዳለባቸው የሚያረጋግጥ የሐኪም ማስረጃ በማቅረባቸው፣ ፍርድ ቤቱ በ20,000 ብር ዋስ ሆነው ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ በቀሪዎቹ ተጠርጣሪዎች ላይ አሥር ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በመፍቀድ ለታኅሳስ 1 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ", "passage_id": "3de3e222fe548df3623c2a2e24411f37" }, { "passage": "በሙስናና ሰብዓዊ መብት ጥሰት የተጠረጠሩት ግለሰቦች ለ2ኛ  ጊዜ  በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት  ቀረቡ ።\nበእነ ጎሃ አጽብሃ መዝገብ በሰብዓዊ መብት ጥሰት 36 እና በእነ ብርጋዴር ጀኔራል ጠና ቁርዲ መዝገብ በሙስና ወንጀል 28 በአጠቃላይ ከ60 በላይ ተጠርጣሪዎች፥ ለ2ኛ ጊዜ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል።\nበሙስና የተጠረጠሩት የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ሰራተኞች እና በሰብዓዊ መብት ጥሰት የተጠረጠሩት የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞችን ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እየተደረገባቸው የሚገኝ ሲሆን፥ከተጠርጣሪዎቹ መካከል እነ ብርጋዴር ጀኔራል ጠና ቁርዲ፣ ብርጋዴር ጄኔራል በረኸ በየነ፣ ብርጋዴር ጄኔራል ጥጋቡ ፈትለአብ እና ብርጋዴር ጄኔራል ሀድጉ ገብረጊዮርጊስ ይገኙበታል።\nየፌዴራል መርማሪ ፖሊስም ተጠርጣሪዎቹ ከደህንነት ቢሮ፣ ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባላቸው የስራ ሃላፊነትና ሚና በሽብር የተፈረጁ ግለሰቦችን በማፈን፣ ስውር እስር ቤት አስገብቶ ኢሰብዓዊ የሆነ ድርጊት እንዲፈጸምባቸው ያደረጉ መሆናቸውንና በተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተሳትፈዋል በማለት ለችሎቱ አስረድቷል፡፡\nፍርድ ቤቱም የፖሊስን የምርመራ መዝገብ ካደመጠ በኋላ ከቀረቡት 36 ተጠርጣሪዎች ውስጥ ሁለቱን በዋስ እንዲወጡ እንዲሁም 16ቱ ተጠርጣሪዎች ደግሞ መንግስት ጠበቃ እንዲያቆምላቸው በማለት ፈቅዷል፡፡ ", "passage_id": "428900100befb81f56118a842f01e53f" }, { "passage": "በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- የሰሜን እዝ ምክትል አዛዥና የሎጂስቲክስ ኃላፊ የነበሩት ሜጀር ጀኔራል ከድር አራርሳ ትናንት ፍርድ ቤት ቀረቡ።እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ሜጀር ጀኔራል ከድር አራርሶ የሰሜን እዝ የጦር መሳሪያ በሕወሓት ልዩ ኃይል እንዲዘረፍ መረጃ ሰጥተዋል በሚል ወንጀል ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፤ ትናንት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል። እንደ ዘገባው፣ ተጠርጣሪው የሰሜን እዝ ምክትል አዛዥና የሎጂስቲክስ ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ በነበረበት ጊዜ ከሕወሐት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ግንኙነት በመፍጠር መረጃ ሲሰጡ ነበር ተብሏል። ከዚህ በፊት በእዙ ስር ያሉ መሳሪያዎችን ከአካባቢው ለማንሳት ሙከራ በተደረገበት ወቅት እንቅስቃሴው እንዲሰናከል ስለማድረጋቸው መረጃ ማሰባሰቡን መርማሪ ፖሊስ ለችሎቱ አብራርቷል። ተጠርጣሪው ከህወሓት ቡድን ጋር ባላቸው ግንኙነት በአድሏዊ አሰራር በተደጋጋሚ የውጭ አገር እድል ይሰጣቸው እንደነበርም ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ገልጿል። በመሆኑም ፖሊስ ለቀሪ የምርመራ ስራዎች 14 ቀን እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል። ተጠርጣሪው በበኩላቸው “በተባለው ጉዳይ ጥፋት የለብኝም ፍርድ ቤቱ በነፃ ያሰናብተኝ” ሲሉ ጠይቀዋል።የግራ ቀኝ ክርክሩን\nያደመጠው ችሎቱ ፖሊስ\nከጠየቀው 14 ቀን\n11 ቀን በመፍቀድ ለታሕሳስ\n26 ቀን 2013 ዓ.ም\nተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013", "passage_id": "b79dd0302fad1d7113c4fc94ff167862" } ]
b13e364ea43412e6c1d98be8a97ddf8b
9381533f96944e97db4dfc88fa8f54f1
ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ግጭት ውስጥ እንድትገባ ወጥኖ የሚሰራ ኃይል መኖሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከቅርብ አመታት ወዲህ የህዳሴው ግድብ መገንባትን ተከትሎ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ግጭት ውስጥ እንድትገባ ወጥኖ የሚሰራ ኃይል መኖሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል።አምባሳደር ዲና እንደገለጹት፤ የምስራቅ አፍሪካን ሰላም የማይሹ ኃይሎች ሱዳን እና ኢትዮጵያ መሃል ክፍተት መፍጠር እንደ ትልቅ ሎተሪ እየተመለከቱት በመሆኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን በትኩረት እየተከታተለው ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያ እና ሱዳን በሚጋሯቸው ድንበሮች ሰሞኑን እየተሰሙ ላሉ ግጭቶች አንዱ የዚህ ኃይል በጉዳዩ አጀንዳውን ለማስረፅ የሚሞክር እንደሆነ የጠቆሙት አምባሳደር ዲና፤ የድንበር ማካለሉ ስራ በትእግስት የሚሰራ ስለመሆኑም አንስተዋል።ባለፈው ሳምንት የተከናወኑ አበይት ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በተመለከተ መግለጫ የሰጠው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የሰባት ሀገሮች ዲፕሎማቶችን የሹመት ደብዳቤ የተቀበሉ እንደሆነ ተገልጿል። አምስት የኤዥያ ሀገራት እና ሁለት የአፍሪካ ሀገራት በኢትዮጵያ የተካሄደው የህግ ማስከበር ዘመቻ በተሳካ መልኩ በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ማስተላለፋቸውም ነው የተገለፀው። የሰባት ሀገራት ዲፕሎማቶችን ሹመት ማስተናገድ ከህግ ማስከበር ጎን ለጎን ኢትዮጵያ በትክክለኛ የዲፕሎማሲ ጎዳና ላይ መሆኗን እና ከዓለም አቀፉ የዲፕሎማሲ ስርአት ጋር በመናበብ እየተንቀሳቀሰች መሆኗን ያጎላ ነው ብለዋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ። ከኢጋድ 38ኛው አስቸኳይ የመሪዎች ጉባኤ ጋር በተያያዘ አባል ሀገራቱ ችግሮቻቸውን ካለማንም ጣልቃ ገብነት በውይይት የመፍታት ባህል የማዳበር አቅጣጫ ተቀምጦ በስኬት መጠናቀቁንም አስረድተዋል። አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በመግለጫቸው፤ በተለያዩ ሀገራት መሪዎችና ተቋማት በተለይም በህግ ማስከበር ዙሪያ በመንግስት ግንዛቤ በሚገባ ያስጨበጡ ስራዎች እንደተሰሩ የተገለፀ ሲሆን፤ እንደ ፊንላንድ ያሉ ሀገራት በህግ ማስከበር ጉዳይ ከመግባባት ባለፈ በቀጣይ ለሚሰሩ ስራዎች የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ፈቃደኝነታቸውን አሳይተዋል።ከዚህ ባለፈም በዚህ ሳምንት ብቻ 327 ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ መሰራቱንም አምባሳደሩ ጠቁመዋል። በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ረገድም ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጋር ስራዎች የተሰሩበት ሳምንት መሆኑን የገለፁት አምባሳደር ዲና ፤የኢትዮጵያ እና ግብፅን የንግድ ግንኙነት የተሻለ ለማድረግም የኢትዮ-ግብፅ የንግድ ስምምነቶችን የተሻለ ለማድረግም ጥረቶች ተደርገዋል ብለዋል። የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ ይሰጥ የነበረውን ዘጠና ሚሊየን ዶላር ተሰረዘ ተብሎ የተወራው ሀሰት ስለመሆኑም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁን የዘገበው ኢቢሲ ነው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37932
[ { "passage": "በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል በአለው ድንበር የነበረው ውጥረት በአሁኑ ወቅት የረገበ ቢሆንም የሱዳን ኃይሎች ድንበር ተሻግረው መሬት መያዛቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።ይሄንን ወረራ የሚያቀነቅኑ የሱዳን የፖለቲካና ወታደራዊ ሊህቃን ቢኖሩም የአካባቢውንና የኢትዮጵያን መረጋጋት የማይሹ ሦስተኛ ወገኖች እንደሚገፉት ተጠቁሟል።ኢትዮጵያ አሁንም ችግሩ በሰላም እንዲፈታ እንደምትፈልግ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ተናግረዋል።\n", "passage_id": "29dc14966eac8c444d9ef9a36a0ebaf1" }, { "passage": "ዩኤኢ በግጭቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ ሰዎች የ5 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እሰጣለሁ ብላለች\nበአፍሪካ ቀንድና በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት መከበርና የኢትዮጵያ አንድነት መከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች(ዩኤኢ) አስታውቃለች፡፡የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት መከበር እንዳለበትና አሁን የተጀመረው ውጊያ መቆም እንዳለበት አስታውቋል፡፡\nሚኒስትሩ ሼክ አብዱላህ ቢን ዛይድ በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት መከበር በአፍሪካ ቀንድ ለሚኖረው ሰላምና መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡\nዩኤኢ አሁን ላይ እየተካሄደ ያለው ውጊያ እንዲቆምና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ በአፍሪካ በተለይም በቀጣናው ካሉ አጋሮቿ ጋር መምከሯን አስታውቃለች፡፡\nየማዕከላዊ መንግስት እና የትግራይ ክልል መንግስት መሪዎች እየተካሄደ ያለውን ውጊያ በማቆም ወደ ንግግር መመለስ አለባቸው ስትል ነው ዩኤኢ የገለጸችው፡፡የኢትዮጵያ መንግስት በሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈጸሙ የሕግ ማስከበር ዘመቻ እንዲጀመር ያዘዘው ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ነበር፡፡\nሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት የሚከለክለውን አለምአቀፍ ህግ ማክበር እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡\nዩኤኢ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት የሚፈናቀሉ ሰዎች በተለይም የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ እንደሚየሳስባት ገልጻለች፡፡ ዩኤኢ በአለም አቀፍ የምግብ ፕሮግራም በኩል በግጭቱ ምክንያት ለተሰደዱትና የሰብአዊ እርዳት ለሚያስፈልጋቸው የሚሊዮን ዶላር እንደምትሰጥም ሚኒስትር አስውቀዋል፡፡\n\n", "passage_id": "ff8dfd78f1dea8dfe38be39b69cef88a" }, { "passage": "የምሥራቅ አፍሪካ አገሮች የኢትዮጵያ መንግሥት በሕወሓት ሕገወጥ ቡድን ላይ እየወሰደ ያለውን ሕግ የማስበር ዕርምጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል መግለጻቸውንና በውስጥ ጉዳይዋ ማንም ጣልቃ መግባት እንደሌለበት መናገራቸውን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ (አምባሳደር) ዓርብ ኅዳር 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙኃን እንደተናገሩት፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ልዑክ፣ በምሥራቅ አፍሪካ አገሮች ጉብኝት ስኬታማ የዲፕሎማሲያዊ ክንውን መፈጸሙን ገልጸዋል፡፡ ልዑኩ ከኬንያ፣ ከሩዋንዳ፣ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና ከኡጋንዳ ፕሬዚዳንቶችና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተገናኝቶ ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ መምከሩንም አምባሳደሩ አክለዋል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት በሰሜን የአገሪቱ አካባቢ እየወሰደ ያለው ሕግ የማስከበር ዘመቻ መነሻና ዓላማውን ሚኒስትሩ ለመሪዎቹ መግለጻቸውን እንዳስረዱም ጠቁመዋል፡፡ ሕወሓት አገራዊ ሪፎርሙን በመቃወም፣ በአገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የሽብር አካላትን ሲደግፍ፣ የሕግ ጥሰቶችን ሲፈጽምና በመጨረሻም የአገር ሉአላዊነት ቀይ መስመርን በማለፉ መንግሥት ሕግ የማስከበር ዕርምጃ እየወሰደ መሆኑን እንዳስረዱም አምባሳደሩ ተናገረዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት እያደረገ ያለው እርስ በርስ ጦርነት ሳይሆን ሕግ የማስከበር ዕርምጃ መሆኑን በማስረዳት የአገሮቹ መሪዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው መደረጉንም አክለዋል፡፡መሪዎቹም የኢትዮጵያ የሰላም ደኅንነት ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም መሠረት መሆኑን በመግለጽ፣ ሕግ የማስከበር ዕርምጃ የአገር ውስጥ ጉዳይ መሆኑን በመጠቆም፣ ማንም ጣልቃ የሚገባበት ጉዳይ አለመሆኑን ለልዑኩ መናገራቸውን ቃል አቀባዩ ገልጸዋል፡፡ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተጨማሪ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደኅንነት ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውም በጂቡቲና በሱዳን በመገኘት ተመሳሳይ ዲፕሎማሲ ሥራዎችን ማከናወናቸውንም አምባሳደሩ ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ  ሁኔታ በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በፓስፊክ አገሮች ያሉ የኢትዮጵያ አምባሳደሮችና ቆንስላዎች፣ ለአገሪቱ መሪዎችና መገናኝ ብዙኃን ስለወቅታዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ ገለጻ ማድረጋቸውን ዲና (አምባሳደር) ተናግረዋል፡፡ ", "passage_id": "436eceeda6c28a90945e8a036753411f" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሱዳን ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሀምዶክ ከሱዳን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ሀገራቸው ከጎረቤት ኢትዮጵያ ጋር ጸብ የመፍጠር ዓላማ የላትም ሲሉ ተናገሩ፡፡ እንደ አል ዐይን ዘገባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሄን ያሉት በሱዳን በነበረው የለውጥ እንቅስቃሴ ወቅት የሀገሪቱ መከላከያ ሰራዊት የቀድሞውን ፕሬዝዳንት ሀሰን አልበሽርን ከስልጣን ካወረደ በኋላ ለተቃውሞ አደባባይ የነበሩ ሰልፈኞች ወደ ቤታቸው እንዲገቡ በማስጠንቀቅ በወሰደው እርምጃ በርካታ ሰዎች የተገደሉበትን አንደኛ ዓመት መታሰቢያ በማስመልከት ከብሔራዊ ቴሌቪዥኑ ጋር ባደረጉት ቆይታ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዘ የተለየ የድንበር ችግር ጉዳይ የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ ቀደም ሲልም በተለያዩ ጊዜያት የነበረ ነው ብለዋል፡፡  ሱዳን ከተለያዩ ጎረቤት ሀገራት ጋር የድንበር ችግሮች ሲያጋጥሟት እንደነበርም አውስተዋል፡፡ “ከኢትዮጵያ ጋር ያለን ግንኙነት በባህል ፣ በታሪክ እና በመልክአ ምድር እና በመልካም ጉርብትና የተሳሰረ ነው” ሲሉም ተደምጠዋል፡፡  እናም “በመካከላችን የሚፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችሉ ስልቶች አሉን” ብለዋል፡፡  በመሆኑም ከሰሞኑ የተፈጠረው ክስተትም በዚህ መንገድ እንደሚፈታ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዶክ ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "2206d1575aa396987f8ad697fc57a9ae" }, { "passage": "በሃገር ውስጥ ወቅታዊ የፀጥታ ችግሮች ሳይገደቡ በአጎራባች ሃገራት የሚታየውን ወቅታዊ ፓለቲካዊና ወታደራዊ እንቅስቃሴ በትኩረት መከታተል እንደሚገባ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ፡፡\nምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ በሰሜን ዕዝ ለከፍተኛ መኮንኖችና ተመጣጣኝ የስታፍ ክፍል ሃላፊዎች ሲሰጥ በነበረው ስልጠና ማጠቃለያ ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ንግግር አድርገዋል፡፡\n\"ኢትዮጵያ ምስራቅ አፍሪካ ከግጭት ነፃ እንዲሆን አበክራ እየሰራች ትገኛለች\" ብለዋል በንግግራቸው፡፡\n”የአጎራባች ሃገራት ውስጣዊ የፓለቲካ ችግሮች ለሃገራችን ሰላም ስጋት ሊሆኑ ስለሚችሉ የሰራዊቱ አመራሮች እነዚህንና መሰል እንቅስቃሴዎችን በሳይንሳዊ መንገድ መተንተን ይገባቸዋል“ ሲሉም ነው ያሳሰሰቡት፡፡\n“በተለይ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ሃብቶቿን ለመጠቀም በምታደርገው ጥረት ጥቅማቸው የተነካባቸው የሚመስላቸው ሃገራት በፕሮጀክት ግንባታዎች ሳይሆን በውስጣችን በሚፈጠሩ የሰላም ችግሮች እንድንጠመድና ግንባታዎች እንዲጓተቱ በእጅ አዙር ሊሰሩ ይችላሉ” ያሉት ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ “የአባይ ተፋሰስ ሃገራት በህዳሴው ግድብ ግንባታና ውሃ አሞላል ዙሪያ እያደረጉት ያለው ድርድር የኢትዮጵያን ተጠቃሚነት የማያረጋግጥ ነው” ብለዋል፡፡\nበመሆኑም ኢትዮጵያ ሃብቷን ለመጠቀም በምትወስደው አቋም ሰላሟን ለማደፍረስና የተቻላቸውን ለማድረግ የሚጥሩ አካላትን ሰራዊቱ ከህዝቡ ጋር በመሆን በንቃት ሊከታተል እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት፡፡\nተቋማዊ ጉዳዮችን በተጨማሪነት ያነሱት ጄኔራል መኮንኑ ተቋማዊ ሪፎርሙን የሚያስቀጥሉ እና የሰራዊቱን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት በተያዘላቸው እቅድና ፕሮግራም መሠረት እየተከናወኑ እንደሚገኝ ማብራራታቸውን መከላከያው በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ አስታውቋል፡፡\n", "passage_id": "65c4169b6c4c2a714e7c5af81c9fd39d" } ]
17b5d047202eeb8d8e04365cf4057514
919b1cace0692a46e34aa1c9083bbdf6
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ወራት 83 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸው ተነገረ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ወራት 83 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 4 ሺህ 359 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን በኦሮሚያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አዲሱ አረጋ አስታወቁ።በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ወራት 83 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ የገቡ ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥ 3 ሺህ 519 ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮች ሲሆኑ 316ቱ ወጣቶች መሆናቸው ተገልጿል። 450ዎቹ ሀገር በቀል ባለሀብቶች እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እና 74 የማስፋፊያ ጥያቄ ያቀረቡ መሆናቸውንም የተጠቆመ ሲሆን፤ ለእነዚህ አልሚዎች 35 ሺህ 920 ሄክታር መሬት ተላልፏል ያሉት አቶ አዲሱ፤ ፕሮጀክቶቹ በሙሉ አቅም ወደ ስራ ሲገቡ ለ313 ሺህ 566 ወጣቶች የስራ ዕድል ይፈጥራሉ ሲሉ አቶ አዲሱ መናገራቸውን የዘገበው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ነው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37944
[ { "passage": "አዲስ አበባ፡- የኦሮሚያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ በሂደት ላይ ያሉ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችን በማጠናቀቅ እና ወደ ሥራ እንዲገቡ በማድረግ በዘንድሮ ዓመት ብቻ ለ129 ሺ ሥራ አጦች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መዘጋጀቱን አስታወቀ። በቢሮው የኢንቨስትመንት ድጋፍና\nቁጥጥር ቡድን መሪ\nአቶ በላይ ዱፌራ\nበተለይ ለአዲስ ዘመን\nእንዳስታወቁት፤ የሥራ አጥ\nችግር ሊፈታ የሚችለው\nኢንቨስተሮች ሲበራከቱ ብቻ\nነው። በመሆኑም ወደ\nክልሉ የሚፈሱ የሀገር\nውስጥም  ሆነ የውጭ ባለሀብቶች ቁጥር እንዲጨምር ለማበረታታት ደንብና መመሪያዎችን በማሻሻል ጭምር እየተሰራ ነው። እስካሁን በክልሉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከወሰዱት 10ሺ742 መካከል ስድስት ሺ አንድ መቶ አስሩ ወደ ማምረት ሥራ መግባታቸውን የጠቀሱት አቶ በላይ ቀሪዎቹ አራት ሺ 300ዎቹ ደግሞ በሂደት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። በሂደት ላይ ያሉት ፕሮጀክቶች በያዝነው ዓመት ተጠናቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን በዚህም ለ129ሺ ሥራ አጦች የሥራ ዕድል ይፈጠራል ሲሉ አስረድተዋል። ደንቡ የተሻሻለበት ዋና\nምክንያት ያለ ኢንቨስትመንት\nእድገት የለም፣ የሥራ\nአጥ ቁጥርንም መቀነስ\nአይቻልም  ተብሎ በመታሰቡ መሆኑን ገልጸዋል። በማሻሻሉም የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን በሚያበረታታና የውጭ ባለሀብቶችን ፍሰት በሚያሳድግ መልኩ ቀደም ሲል የነበረውን የኢንቨስትመንት ሕግና ደንብ ተቃኝቷል። አቶ በላይ እንዳሉት ከዚህ በፊት 141/2004 የሚባል የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ደንብ የነበረ ቢሆንም ሀገሪቱ እያደገች ካለችበት ሁኔታ ጋር በማጣጣም የኢንቨስትመንት ፍሰቱ ወደ ክልሉ እንዲመጣ ለማመቻቸት የክልሉ መንግሥት አዋጅና ደንቡን እንደገና አይቷል።በዚህም በከተማና በገጠር ተከፋፍሎ ሲደራጅና ሲደገፍ የነበረውን ኢንቨስትመንትም ወደ አንድ እንዲመጣ አድርጓል። ደንብ 141 መመሪያ 1/2004 ከግብርና እና ከማይክሮ ኢንተርፕራይዝ ወደ ኢንቨስትመንት የተዘዋወሩ ባለሀብቶችና በተለያየ አቅጣጫ ንብረት ያፈሩ ሴቶችን በልዩ ሁኔታ የሚያበረታታ እንዳልነበረ ጠቅሰው፣ አሁን ይህ ደንብ ከዓመት ዓመት ንብረት እያፈሩ ያሉ ገበሬዎችን ወደ ኢንዱስትሪ፣ ማይክሮ ኢንተርፕራይዞችንም ወደ መካከለኛና ወደ ኢንቨስትመንት እንዲሸጋገሩ ያደርጋል።በአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ባለሀብት በኢንቨስትመንት ውስጥ ትልቅ ድርሻ እንዲኖራቸው ያደርጋል፤ የውጭ ባለሀብቶችንም ይጋብዛል። አቶ በላይ እንዳሉት\nበ2010 ዓ.ም\nበሀገሪቱ ከነበረው የሰላም\nሁኔታ ጋር በተያያዘ\nኢንቨስትመንት የቀነሰበት ሁኔታ\nነበር።ከ2011 ጀምሮ\nግን ወደ ቦታው\nተመልሷል።አሁንም ያለው ፍሰትም\nጥሩ ነው።በርካታ ባለሀብቶች\nለማልማት እየጠየቁ ሲሆን\nመንግሥትም ድጋፍ እያደረገ\nእና መሬት እየተሰጠ\nይገኛል ብለዋል።አዲስ ዘመን ጥቅምት 16/2012አልማዝ አያሌው", "passage_id": "0bd1a0437c706c0500c315bd7b9909c8" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል 5 ሺህ ግንባር ቀደም አርሶ እና አርብቶ አደሮችን ኢንቨስትመንትን ጨምሮ በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ ለማሰማራት የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁ ተገለፀ።በሀገሪቱ ግንባር ቀደም አርሶ እና አርብቶ አደሮችን  በመለየት በተለያዩ ሽልማቶች ማበረታታት ከተጀመረ ዓመታት አልፏል።በዚህ ውስጥ በምርት፤በሃብት እና በቁጠባ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ፤ ከራሳቸው ባለፈ በሀገር ደረጃ በሚመዘን አሻራቸው እየተለዩ በሜዳሊያ፣ ዋንጫ እና ሌሎች ማበረታቻዎች እና ሽልማቶች እየተሰጣቸው ለሌሎችም አርዓያ ይሆኑ ዘንድ የታሰበው ፕሮግራም ዛሬም ቀጥሏል።ይሁን እንጂ  በግንባር ቀደሞቹ የተሰበሰበው ጥሪት ትርጉም ባለው መልኩ ለሌሎች በሚተርፍ፣ ስራን ፈጥሮ ለሌሎች አያሌ ወጣቶች ሀብት ማፍሪያነት በሚውል መልኩ እንዳልተሰራበት  ይነገራል።ለምሳሌ በኦሮሚያ ክልል ግንባር ቀደም አርሶ እና አርብቶ አደር ተብለዉ ከብዙዎች የክልሉ አርሶ አደሮች የላቀ ዉጤት በማስመዝገብ  ለዚህ ሽልማት የበቁት ቁጥራቸው 1 ሚሊየን መድረሱን የክልሉ የገጠር ክላስተር ቢሮ መረጃ ያመላክታል።ይህን ሃብት  በተቀናጀ መልኩ ደምብ እና ስርዓት ተበጅቶለት ሌሎችን ቀጥረው ወደሚያሰሩበት አሰራረ ማሳደግ ባለመቻሉ  ክልሉ ቁጥራቸዉ ከፍ ባሉት ስራ አጦች እንዲሞላ መንገድን የከፈተ መሆኑም ይነገራል።በኦሮሚያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪ ዶክተር ግርማ አመንቴ ከፋና ብሮድካሰቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ ካሁን በኋላ ይህ መሰል አሰራር አይቀጥልም ብለዋል።ለአርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ሜዳሊያ ከመሸለም በዘለለ ቀጣይነት ያለው ነገር ማድረግ ይገባል በማለት።የክልሉን ህብረተሰብ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ አንድ አቅጣጫ የተቀመጠው ግንባር ቀደም አርሶ አደር ተብለው የተለዩትን ኢንቨስትመንትን ጨምሮ በንግድ እና አገልግሎት ዘርፎች  ላይ ለማሳተፍ ይሰራልም ብለዋል።በዘንድሮ ዓመት ብቻ 5 ሺህ አርሶ አደሮችን ወደዚሁ ለማስገባት ቅድመ ዝግጅቴን አጠናቅቄያለሁ የሚለው ክልሉ፥ ሂደቱ የተሳለጠ እና ከአሰራር ችግር የፀዳ እንዲሆን የክልሉን ኢንቨስትመንት ደምብ የማሻሻል ስራ መከናወኑንም አስታውቋል።አርሶ እና አርብቶ አደሮቹም ቢሆኑ ወደዚህ ስራ ሲሰማሩ በተለያዩ ህጋዊ መስመሮች ማለፍ ሊጠበቅባቸው እንደሚችል በመጥቀስ   ለዚህም በግብርና ቢሮ የአግሪ ቢዝነስ ዳይሬክቶሬት ተቋቁሟል ብለዋል ዶክተር ግርማ።ግንባር ቀደም አርሶና አርብቶ አደሮችን ኢንቨስተመንት፣ በንግድና አገልግሎት የማሰማራት እቅዱ 50 ሺህ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል እንደሚፈጥር ከወዲሁ ተገምቷል።ለስኬቱም የተለያዩ ሴክተሮች የ50 ቀን እቅድ አውጥተው እየሰሩበት መሆኑ  ነው የተገለጸው።እንደ ዶክተር ግርማ ገለፃ፥ እቅዱ  የአርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን ህይወት ከማሻሻሉ ባለፈ 50 ሺህ የሚሆኑ  ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።በአፈወርቅ አለሙ", "passage_id": "78e32098b32fa5e7fb3fcdee2556eee8" }, { "passage": "ጅግጅጋ፡- በ2011 በጀት ዓመት በሶማሌ ክልል 472 የአገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች 1ነጥብ12 ቢሊዬን ብር ኢንቨስት ማድረጋቸው ተገለጸ። ክልሉ ያለውን እምቅ የኢንቨስትመንት አቅም ተጠቅመው ከራሳቸው አልፈው ለክልሉም ሆነ ለአገር የሚተርፍ ስራ እንዲያከናውኑም ለባለሀብቶች ጥሪ ቀርቧል። የክልሉ የኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዲአሲስ መሐመድ ለአዲስ ዘመን\nጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በ2011 በጀት ዓመት በክልሉ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታና ማበረታቻ በመጠቀም 1ነጥብ12 ቢሊዬን ብር ያስመዘገቡ\n472 የአገር ውስጥ ባለሃብቶች፣ ዳያስፖራዎችና የውጭ ባለሃብቶች በክልሉ ኢንቨስተመንት ተሰማርተዋል። ይሄም ከ2010 በጀት ዓመት\nአፈጻጸም ከፍተኛ ብልጫ አለው። እንደ አቶ አብዲአሲስ ገለጻ፤ እንደ አገር በተለይም በክልሉ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በክልሉ\nየተፈጠረው ሰላም ለኑሮ ብቻ ሳይሆን ለኢንቨስትመንቱም ትልቅ እድል ይዞ መጥቷል። በተለይም የክልሉ ተወላጅ ዳያስፖራዎች ተሳታፎ\nአድጓል። በዚህም የባለሃብቶች ቁጥር በ2010 በጀት ዓመት ከ200 ያልበለጠ ቢሆንም፤ በ2011 በጀት ዓመት ወደ 472 አድጓል።\nእነዚህ ባለሃብቶችም በድምሩ 1ቢሊዬን 126ሚሊዬን 191ሺ 967 ብር ያስመዘገቡ ሲሆን፤ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎችም ተሰማርተዋል።\nየክልሉ ኢኮኖሚ በግብርናና እንስሳት ሃብት ላይ የተመሰረተ እና ክልሉም እንስሳትን ወደውጭ\nከሚልኩ አምስት ክልሎች አንዱ መሆኑን የሚናገሩት አቶ አብዲአሲስ፤ ባለሃብቱም በአካባቢው ያለውን እምቅ ሃብት መጠቀም በሚያስችሉ\nዘርፎች እንዲሰማሩ መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም የተለያዩ ፋብሪካዎችን ከመክፈት ባለፈ፤ በግብርና ስራ ብሎም በእጣንና ሙጫ ምርት\nኢንቨስትመንት ላይ መሰማራታቸውንም ጠቁመዋል። አቶ አብዲአሲስ እንደሚሉት፤ በበጀት ዓመቱ በክልሉ ስለሚኖረው የኢንቨስትመንት አሰራር ለባለሃብቶች\nግንዛቤ በማስጨበጥ ወደስራ የተገባ ሲሆን፤ በለሃብቶችም ማበረታቻ አግኝተው በተሰማሩበት ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የፋብሪካ\nእቃዎች፣ ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎችን ጭምር ከቀረጥ ነጻ እንዲያስገቡ ተደርጓል። ቀደም ሲልም ሆነ በበጀት ዓመቱ መሬት ወስደው\nበትክክል እየሰሩ ያሉትን የበለጠ ለማበረታታት፤ ወደስራ ያልገቡትንም በአሰራር መሰረት መስመር ለማስያዝ ሰፊ የድጋፍና ክትትል ስራዎች\nተከናውነዋል። በዚህም መሬት ይዘው ለዓመታት ሳያለሙ ያስቀመጡ ባለሃብቶች በመገኘታቸው መሬቱ ተወስዶ ለመንግስት\nእንዲመለስና ወደ መሬት ባንክ እንዲገባ ተደርጓል። ለምሳሌ፣ በሸበሌና ሲቲ ዞኖች ለኢንቨስትመንት ከተሰጠ 110 ሺ ሄክታር መሬት\nውስጥ መልማት የቻለው 26ሺ ሄክታር መሬት ብቻ ነበር። በተደረገ የክትትልና ግምገማ ስራም ሳይለማ በግለሰቦች እጅ የከረመው ከ80ሺህ\nሄክታር በላይ መሬት ተመላሽ ሆኗል። ለውጡን ተከትሎ በክልሉ የታየው ሰላም የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ\nማሳደሩን የሚናገሩት አቶ አብዲአሲስ፤ የኢንቨስትመንቱ መጠናከር ለክልሉ ብሎም በአገር ጉልህ ፋይዳ ያለው መሆኑን ተገንዝቦ ለኢንቨስትመንቱ\nምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር መስራት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል። የክልሉ መንግስትም ለልማት ወደክልሉ ለሚሄዱ ባለሃብቶች ሕግና መመሪያ በሚፈቅደው ልክ እንደየኢንቨስትመንቱ ባህሪ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ መሆኑን በመጠቆም፤ ባለሃብቶችም የሶማሌ ክልል ከእንስሳትና የደን ሀብቱ ባለፈ ገናሌና ዳዋን የመሳሰሉ ዓመቱን ሙሉ የሚፈስሱ ወንዞች ያሉበት መሆኑን በመገንዘብ፣ ብሎም በክልሉ ያለውን ሰላም፣ እምቅ የኢንቨስትመንት አቅምና የሚደረገውን ማበረታቻ ተጠቅመው ራሳቸው እንዲጠቀሙና አገርንም እንዲያለሙ ጥሪ አቅርበዋል።አዲስ ዘመን ነሀሴ 13/2011\nወንድወሰን ሽመልስ", "passage_id": "aca01ac7c0d39d55cb20d430dc8f9f63" }, { "passage": "በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊየን በላይ ስራአጥ ዜጎች እንደሚገኙ የፌዴራል የስራ እድል ፈጠራ ኮሚሽን ገልጿል፡፡በተያዘው የበጀት ዓመት ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ከተመደበው 10 ቢሊየን ተዘዋዋሪ ፈንድ ውስጥ ከ9 ቢሊየን ብር በላይ መሰራጨቱም ታውቋል፡፡በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሚመራው የኢፌዴሪ የስራ እድል ፈጠራ ብሄራዊ ምክር ቤት በሃገሪቱ ባሉ መልካም አጋጣሚዎች ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ምክክር ባደረገበት ወቅት ተገልጿል፡፡በኢትዮጵያ ከ53 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ለስራ ብቁ ቢሆኑም ከነዚህ ዉስጥ 20 በመቶ የሚሆኑት ስራአጥ ናቸውም ተብሏል፡፡በሚቀጥሉት አመታትም በስራ እድል ፈጠራ ላይ ከፍተኛ ሚና ያላቸው የዘርፉ ተቋማት ትኩረት ሰጥተው ካልሰሩበት በአውሮፓውያን የዘመን ቀመር 2030 ቁጥሩ ከ10 ሚሊየን ወደ 18 ሚሊየን ሊያሻቅብ ይችላል፡፡ባለፉት ሁለት እና ሶስት ዓመታት በአማካይ በዓመት ለ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉ ተጠቁሟል፡፡ እንደ ኢትዮጵያ የሳይንስ አካዳሚ ጥናት በሃገሪቱ 1 ነጥብ 6 ሚሊየን የመንግስት ሰራተኞች ሲኖሩ ይህም በሃገሪቱ ካለው የስራ እድል አንጻር 4 ከመቶ ብቻ ነው፡፡ ", "passage_id": "543b2e619b09e8be116eaaa59b5d40c0" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሀረሪ ክልል ከ300 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመረቁ።በምረቃ ስነስርዓቱ ወቅት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሩ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሚስራ አብደላና ሌሎች የካቢኔ አባላትና ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወካዮችም ተገኝተዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በስነስርዓቱ ወቅት ፕሮጀክቶቹ የክልሉን ህብረተሰብ የልማት ጥያቄ ከመመለስ አንጻር ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ተናግረዋል።ከፕሮጀክቶቹ መካከልም ከታቀደላቸው የጊዜ ገደብ ቀድመው እንደተጠናቀቁ ጠቅሰው በቀጣይም ይህ ተግባር አጠናክሮ ከመቀጠል አንጻር በትኩረት ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።ከ200 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የመንግስታዊ ተቋማት የቢሮ እጥረት ለመቅረፍ የሚያስችል እና ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር የተገልጋዩን እርካታን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ብለዋል።ከዚህ በተጨማሪም አርሶ አደሩ ምርቱን ለተጠቃሚ ማድረስ የሚያስችለው የመንገድ ፕሮጀክት ስራን በይፋ አስጀምረናል ብለዋል።ለፕሮጀክቱ መሳካትም የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ እንደነበረ ጠቁመው በቀጣይም ይህ ተግባር አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።በመሆኑም ተግባራዊ የሆኑ ፕሮጀክቶች የክልሉን ህዝብ ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥና የልማት ጥያቄዎችን የሚመልስ መሆኑን ተናግረዋል።የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሚስራ አብደላ በበኩላቸው በእለቱ ከመንገድ መሰረተ ልማት እንዲሁም በትምህርት በግብርናና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ ተችሏል።እንዲሁም በከተማው ኤረር በር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ እስከ ገጠሩ ኤረር ወልዲያ ድረስ የሚዘልቀው የ13 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የመንገድ ፕሮጀክትም በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።ይህም የህብረተሰቡ ከመሠረተ ልማት እና ከአገልግሎት ጋር በተያያዘ ሲያነሳው የነበረውን ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል።በቀጣይም የክልሉ ህዝቡ ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሰራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።በእለቱ የአፈጉባኤ ህንፃ፣የትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክት፣ ዲጂታል ላይብረሪ፣ አፈ-ጉባኤ መሰብሰቢያ ዘመናዊ አዳራሽ ግንባታ ፕሮጀክት፣ ዶሮ እርባታ ማዕከል ማስፋፊያ እንዲሁም የመንገድና እና የመብራት ፕሮጀክት በእለቱ የተመረቁ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ከክልሉ ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።", "passage_id": "6e0abaee4095e432e790977c12d45bba" } ]
4744d84045051e757dbc087a5f13d311
d38745a7b8d8c7ddb26b0394ab1593d6
አገርን ከብተና ያዳነው ርምጃና ቀሪ የቤት ስራዎች
ጽጌረዳ ጫንያለው በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ ከ113 በላይ ግጭቶች መከሰታቸውን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ መጥቀሳቸው ይታወሳል። የነዚህ ግጭቶች ዋነኛ ዓላማ ደግሞ አገርን መበተንና የማያባራ የእርስ በርስ ግጭት መፍጠር እንደነበር ይገለጻል። ሆኖም የብልጽግና ፓርቲ ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ እንደገለፀው፤ መንግስት በወሰዳቸው ጠንካራ እርምጃዎች ሃገርን ከብተና ማዳን ተችሏል። የፖለቲካ ሳይንስ ምሁራንም ይህ እሳቤ ትክክል መሆኑን በመጥቀስ፤ በቀጣይ በርካታ የቤት ስራዎች እንዳሉ ይጠቁማሉ።በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና አለማቀፍ ግንኙነት መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ እንደሚናገሩት፤ አገር በብዙ መንገዶች ልትበተን እንደደረሰች የሚያሳዩ ምልክቶች ነበሩ። ከእነዚህ መካከልም እያንዳንዱ ክልል ከማዕከላዊ መንግስት ጋር ያለው ግንኙነት የተራራቀ መሆኑ አንዱ ነው። ህወሓት ወታደራዊ፣ የፋይናንስ ዘርፍና የፖለቲካ ግንኙነቱን ከፌደራሉ መንግስት በወጣ መልኩ ሲያከናውን ታይቷል። ስልጣንና ኃላፊነቱ የፌደራል መንግስት ሆኖ ሳለም በራሱ በአደባባይ የክልል መከላከያ ማቋቋሙን ሲናገር ነበር። ምርጫ ማካሄዱ፤ ከኢትዮጵያውያን ይልቅ የሌሎች አገራት ዜጎች ይሻሉኛል ማለት መጀመሩም ሌላው በመርህ ብቻ ሳይሆን በተግባርም አገር የማፍረስ ዘመቻ መኖሩን አመላካች ነበር። እንደ ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ገለጻ፤ የህወሓት ጁንታ 27 ዓመት ሙሉ ከትጥቅ እስከ ሀሳብ ማስታጠቅ ድረስ ሰርቷል። በክልሎች ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖርም አድርጓል። ከኢትዮጵያ ክልልነት ውጪ አገር እንመሰርታለን ብለው የሚነሱ አካላትን ስፖንሰር ሲያደርግም ቆይቷል። ይህ ደግሞ አገር የማፍረስ እንቅስቃሴ እንደሆነ የሚያነሱት ረዳት ፕሮፌሰሩ፤ የቡድኑን የሥነልቡና፤ ቁሳዊና የፋይናንስ አቅሙን ማዳከም መቻሉ ጥሩ ጅማሮና አገርን ከትልቅ አፍራሽ ሀይል መታደግ ነው። ሆኖም ጅማሬ እንጂ ፍጻሜ አይደለም። ምክንያቱም የጽንፈኛው ቡድን ተላላኪዎች፣ በስልጣን የቆዘሙ ሀይላት በተለያዩ ክልሎች ይገኛሉ። ነገ ችግርም የሚሆኑበት አጋጣሚ አለ። የፌደራል መንግስት አሁን እየሰራ ያለው ስራ እንዳለ ሆኖ በዚህ ሂደት የሚረሱ ይኖሩና በማን ይነካኛል ስሜት የህወሓትን ጁንታን ሊያዩ ስለሚችሉ፣ የዚያን ጊዜ ደግሞ ይህንን ያህል ዋጋ አገር እንድትከፍል ትሆናለች የሚሉት ረዳት ፕሮፌሰሩ፤ የህወሓት ጁንታ መንግስትን ልፍስፍስ አድርጎ መሳሉና በይፋም ከሌሎች አገራት ጦር መሳሪያ መግዛትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማድረጉ መታየቱን ገልጸዋል። ዛሬም ይህ አስተሳሰብ ካልተገራ የአገር መበተን እርሾ ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋል ይላሉ። በደብረብርሀን ዩኒቨርሲቲ የስነዜጋና ስነምግባር መምህርና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ አቶ ሀሳቡ ተስፋ በበኩላቸው፤ ከ1983 በኋላ ያለው የፌደራል መንግስት አደረጃጀት ብሔር ተኮር መሆኑ በራሱ አገር ለማፍረስ መሰረት እንደነበር ያነሳሉ። የጋራ ማንነቶችና ታሪኮች ኮስሰው ልዩነቶች እንዲጎለብቱ አድርጓል። የአንድነት ቀን ሳይሆን የልዩነት ቀኖች እንዲከበሩም እድል ሰጥቷል። አካባቢያዊ ማንነቶች ጎልብተው የአንተ አይደለም አስተሳሰቦችም ቦታ አግኝተዋል። በዚህም አገር ለመበተን ደርሳ እንደነበር ይናገራሉ። ኢትዮጵያ የምትባለው አገር ብትኖርም ኢትዮጵያዊነት ሳይሆን አካባቢያዊነት የተለየ ትኩረት እንደተሰጠው የሚናገሩት መምህር ሀሳቡ፤ ህዝቦችም ሆነ መንግስት አገር ላይ ሳይሆን አካባቢ ላይ የሚደርስ አደጋን እየለየ እሳት እንዲያጠፋም አስገድዶታል። ስለሆነም አሁን የተጀመረው ሥራ አገርን ከመበተን ታድጓል ይላሉ። ነገር ግን ብሔርን መሰረት ያደረገ የፌደራል ሥርዓት በህግ ጭምር መፍትሄ ካላገኘ መልሶ አገር የመበተኑ እንቅስቃሴ የሚያገረሽ እንደሚሆን ይገልጻሉ። አንድን አካል በማስወገድ ብቻ አገር ማዳን አይመጣም። አብዲ ኢሌ በሱማሌ ክልል ሲያደርስ በነበረው የጥፋትና የመከፋፈል ሥራ ወቅት የተወሰደው እርምጃ የዚህ ማሳያ ነው። ከዚህ ያልተማረው የህወሓት ጁንታም ብቻዬን አገር ካልመራሁ ብሎ ለማፍረስ ሲጣጣር ሴራው መምከን ችሏል። ይሁን እንጂ ከህወሓት ጁንታ በኋላም ሌላ ላለመምጣቱ ማረጋገጫ የለም። እናም አሁን የተደረገው አገርን ከመበተን የማዳን ጅማሮ እንጂ ፍጻሜ አይደለም። ምክንያቱም አገር መመስረት ህገ መንግስታዊ መብት ነው። በመሆኑም ሥራው በህገ መንግስት ምላሽ ካላገኘ አገር እንደማይድን ይናገራሉ።መፍትሔው ጅምሩን እያደነቁ የወደፊት የአገራዊ አንድነት እየሸረሸሩ የሚሄዱ ጉዳዮችን ከመሰረቱ እያደረቁና እየፈቱ መሄድ እንደሆነ የሚገልጹት ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው፤ ፖለቲካዊ፣ ህገመንግስታዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ማለትም ማህበረሰቡን በትምህርት በስነልቦና መስራት ይገባል። የፖለቲካና የስነልቦና ትርክቶች አንድነትን ለማምጣት በሚያስችሉ ሁኔታዎችን መቅረጽ ያስፈልጋል። የህወሓት ጁንታ ኢትዮጵያዊነትን በሚያቀነቅን ህዝብ የተጠላ በመሆኑ ህዝብ እንቢ ብሎት ለመንግስት እድል እንዲሰጠው ሁሉ በህዝብ መወደድ ላይም መስራት ይገባል ይላሉ። እንደ ረዳት ፕሮፌሰሩ ገለጻ፤ የለውጡ መንግስት በድርድር ቢሆን ኖሮ ከህወሓት ጋር አንድም ጥይት አይታኮስም። ነገር ግን ህወሓት የግራ ዘመሙ ጉዳይ የተጠናወተው በመሆኑ በዚህ መሸነፍ አልቻለም። ስለሆነም በቀጣይም አፈንጋጩንና ኢትዮጵያን የሚጠላውን በሚገባው ቋንቋ ማናገርና አገርን ማዳን መሰረታዊ ጉዳይ መሆን አለበት። ለስርዓቱም ሆነ ለህዝብ አደጋ የሆነ አካልን መቅኔውን መስበር ከተቻለ አገር አዳንን ሊያስብል ይችላል። አገርን ከማዳን አንጻር የተጀመረው ነገር ህዝብ ከአመጽ አይነኬ የሚባለውን ሁሉ እንደሚያሳፍር የታየበት ነው። ስለዚህም ይህንን ማስቀጠልና ትርክትንማስተካከል፣ የጋራ ራዕይን በትምህርት መገንባት፣ የፖለቲካ ትርክቶችን ገዳይ አስገዳይ ፣ በዳይ አስበዳይ ከሚለው ማውጣት፤ የጋራ የሚያደርጉትን ማጉላትና ልዩነቶችን መቀነስ እንዲሁም የነበረ ማውደምን ሳይሆን ጥሩውን መምረጥንም መማርና በተግባር ማሳየት ላይ መስራት እንደሚገባም ያስረዳሉ። አቶ ሀሳቡ እንደሚሉት ደግሞ፣ ህወሓትን ማጥፋት አገርን በዘላቂነት ከብተና የሚያድን ተደርጎ መወሰድ የለበትም። መፍትሄው ተመሳሳይ ሀሳብ ያላቸውን አካላት አሁን በተጀመረ መልኩ መግታት ነው። የአገረ መንግስት ግንባታውንም እንደ ብልጽግና ውህድ ፓርቲ መስርቶ ሁሉም ዜጋ ለአገር ያገባኛል እንዲል ማስቻል ይገባል። እናም ይህ ተግባር በቋሚነት ውጤት በሚያመጣ መልኩ መቀጠል ይኖርበታል። ከ27 ዓመት በላይ በስነልቦና የተለያየ ህዝብ ወደ ጋራ ታሪኩ መመለስ ላይ መስራትም ይገባል። በችግር ውስጥ ተሆኖ የመጣውን ለውጥ ፍርደ ገምድል ሳንሆን መደገፍና አንድነት ላይ መስራት ከሁሉም እንደሚጠበቅ አስረድተዋል። በተለይ ግን ለሁሉም መፍትሄ የሚሆነው ህገመንግስቱን በታኝ ሳይሆን ከብሔር አስተሳሰብ ወጥቶ በአንድነት ውስጥ ልዩነትን መጥኖ እያስተናገደ ማሻሻል ሲቻል እንደሆነ ይገልጻሉ። ቀደም ሲል በደርግ ሥርዓት አገር ለማፍረስ የተሞከሩ ተግባራት ታይተዋል። ከእነዚህ ውስጥም አገር ሊያፈርስ የሚችሉ ውሳኔዎች መኖራቸው የመጀመሪያው ነው። በፍርድ ቤት እንዲገደሉ ያልተወሰነባቸውን 12 ጀነራሎችን ጸረ አብዮት በማለት መረሸናቸው ለአገር መከታ የሚሆኑትን ከማሳጣቱም በላይ አገርን ለብተና የዳረገ ነበር። አገር መፍረስም መዳንም የሚችለው በእሳቤና በህግ ወይም በሀሳብ ፍሰት መሆኑ ይታወቃል። ስለዚህም በቀጣይ ሊመጡ የሚችሉ ብዙ ቂም ያረገዙ ነገሮች ይኖራሉና እነርሱን መመለስ በሚያስችል መልኩ መሆን እንዳለበት ምሁራኑ ይናገራሉ።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37980
[ { "passage": "– ከ670 እስከ 700 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል – 400 አፈናቃዮች በቁጥጥር ሥር ውለዋል አዲስ አበባ፡- ህግና ስርዓትን ማስከበርና በህግ የሚጠየቅን አካል እንዲጠየቅ የማድረግ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ። የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራው ሥራ 800 ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸው ተጣርቷል፤ 400 ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ተፈናቃዮችን ለማቋቋም ከ670 እስከ 700 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት 5ኛ ልዩ ስብሰባ ትናንት ሲካሄድ፣በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች ያሉበትን ሁኔታ የተመለከተው የሱፐርቪዥን ቡድን ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል። የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ፣ ቡድኑ ያቀረበው ሪፖርት፤ ሚዛናዊ፣ የተፈናቃዮችን ድምጽ ያሰማና ሁኔታቸውን ያሳየ መሆኑንም ጠቁመዋል። ያልታዩ አካባቢዎች በቀጣይ እንደሚታዩም አመልክተዋል። ዓለም ያስደመመ ለውጥ እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታ ውሰው፤ በአንጻሩ፤ አንገት የሚያስደፋ መፈናቀል፣ ሞትና ግጭት መኖሩ አሳፋሪ መሆኑን በማንሳት ድርጊቱን ኮንነዋል። ዜጎች ወጥተው የሚገቡበት ሰላማዊ ማዕቀፍ ማረጋገጥ ይገባልም ብለዋል። በለውጥ ወቅት አገር ሲመራ በርካታ ተግዳሮቶች ይገጥማሉ ያሉት አቶ ደመቀ፤ ችግሩን ማስተካከል የሚያስችል፣ የህዝብ ተጠ ቃሚነትን የሚያረጋግጥ ሥራ በመስራት ለውጡ ጥልቀት እንዲኖረው ይደረጋል ብለዋል። ህዝቡን ከመፈናቀልና መሰል ስጋት አላቅቆ ወደ ለውጥ ግስጋሴ የማስገባት ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው የገለጹት። የችግሩን ባህሪና ስፋት የሚመጥን ሥራ እንደሚሰራ፣ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግረዋል። የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል፤ የተፈናቃዮች ቁጥር የማጥራት ሥራ መቀጠሉን በመጠቆም፤ ተጠያቂ መሆን የሚገ ባቸው ሰዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራው ሥራ 800 ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸው ተጣርቶ ማለቁንና 400 ሰዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለ ተናግረዋል።ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ ያለመስጠት የፖለቲካ አመለካከት ችግር እንዳለም አንስተዋል። ‹‹እንዲህ ዓይነቱን ሁኔታ እያስታመምን አንቀጥልም፣ አመራሮችም የተሰጣቸውን ኃላፊነት ባግባቡ ሊወጡ ይገባል›› ሲሉ አሳስበዋል። ተጠርጣሪዎችን በህግ ጥላ ስር ማዋል ካልተቻለ ተፈናቃዮችን ወደ ቦታቸው መመለስ አዳጋች ነው ሲሉ ስጋታቸውን ጠቁመዋል። በአንዳንድ አመራሮች ተገቢ ያልሆኑ ጥያቄዎች እንደሚነሱና አመራሮችም መጠየቅ እንዳለባቸው አንስተዋል። ከአልሚ ምግብና ሌሎች ከሰብዓዊ ድጋፍ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጉዳዮች ላይም ችግሩን የሚመጥን ሥራ እንደሚሰራ አመልክተዋል። ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት እንቅስቃሴ መከፈቱንም ነው የጠቆሙት። ክረምት ከመግባቱና የተፈናቃይ ዜጎች ህይወት ለአደጋና ስጋት እንዳይጋለጥ ወደ አካባቢያቸው የመመለስ ሥራው በፍጥነት እን ደሚሰራም ገልጸዋል። ከጦር መሳሪያ ጋር ተያይዞ ልቅ ነገር ስለሚታይ ሥርዓት ማስያዝ ያስፈልጋል ብለዋል። ሀብትና ንብረት የወደመባቸው ዜጎችን መረጃ በመያዝ ከባንኮችና ከብድር ተቋማት ጋር በቅርበት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የጤና አገልግሎት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን በመጠቆምም፤ ጉዳት የደረሰባቸው 215 ጤና ኬላና 12 ጤና ጣቢያዎች የማሻሻያ ሥራዎች እንዲሰሩ መለየታቸውንም ለምክር ቤቱ አስረድተዋል። የተለያዩ የእርሻ መሳሪያዎች ለማቅረብና የሙያ ድጋፍ ለመስጠት ትኩረት መደረጉንና የተጀመረው እርቀ ሰላም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ወይዘሮ ሙፈሪሃት ገልጸዋል። ጊዜያዊና ዘላቂነትን ያጣመረ መፍትሄ ይተገ በራል፣ በአገር አቀፍም ዘላቂና አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን ይሰራል ብለዋል። ብሄራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ፤ ከ2009 ዓ.ም አንስቶ ሳያቋርጥ የሰብዓዊ ድጋፍ እየቀረበ ቢገኝም የተጓደሉ ነገሮች መኖራቸውን አንስተዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ የተፈናቃዮች ቁጥር በመጨመሩ የተፈጠረ ችግር መሆኑን ተናግረዋል። የመንገዶች መዘጋት እርዳታ የሚያመላልሱ ተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ገድቦ እንደነበርም አስታውቀዋል። የአልሚ ምግብና የግብአት አቅርቦት ችግር መኖሩንና ክልሎች የሚችሉትን ያለማድረግ ችግር እንዳለም አንስተዋል። ለመልሶ ማቋቋም ሥራው ከ670 እስከ 700 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅት ባለፉት ሁለት ወራት ትግበራ በሦስት ዙር ሊመለሱ ይችላሉ ተብለው ከተለዩ ተፈናቃዮች 760ሺ ገደማ (ሰባት መቶ ስልሳ ሺ) ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ ማድረግ መቻሉንም ጠቁመዋል። የትምህርት ሚኒስቴር ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በበኩላቸው፤ በዜጎች መፈናቀል ምክንያት ትምህርት ላይ ከፍተኛ ችግር መፈጠሩን በመጠቆም፤ የትምህርትና የአልባሳት ቁሳቁስ በማቅረብ ባሉበት ቦታ ትምህርታቸውን እንዲ ከታተሉ የተደረገ ወቅታዊ መፍትሄ እንዳለ ጠቁመዋል። ችግሩ ሙሉ ለሙሉ የሚፈታው ለተፈናቃዮች እልባት ተሰጥቶ ወደ አካባቢያቸው መመለስ ሲችሉ፣ የወደሙ ትምህርት ቤቶች ሲጠገኑና መምህራንም ሲመለሱ መሆኑን ነው ያነሱት። ችግሩ የትምህርት ጥራት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያስከትልም አንስተዋል። የከፍ ተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች እያቀረቡ ያሉት የቦታ ቅያሪ ጥያቄ ችግሩን ስለሚያባብሰው ተቀባይነት እንደሌለውም ተናግረው፤ አንጻራዊ ሰላም በመስፈኑ ተማሪዎች ተመልሰው ትምህር ታቸውን እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። የሱፐር ቪዥን ቡድኑ በሪፖርቱ፤ የዜጎችን ሰብዓዊ መብት የጣሱ፣ህይወት ያጠፉ አካል ያጎደሉና ንብረት ያወደሙ በአፋጣኝ ሊጠየቁ ይገባል ሲል አመልክቷል።ዘላቂ ሰላምን በማረ ጋገጥ ዜጎች በየቀዬአቸው ያለስጋት የሚኖሩበትን ሁኔታ መፍጠርም ይገባል። ጉዳዩ ተፈናቃይ ዜጎችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችል የተለየና የተቀናጀ ዕቅድ እንዲወጣና እንዲተገበርም አሳስበዋል። የሱፐር ቪዥን ቡድኑ 24 አባላትን ያቀፈና ቋሚ ኮሚቴዎች የተወከሉበት ነው። ጥናቱ በትግራይ፣ በደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች፣ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች የተካሄደ ሲሆን፤ መረጃው በ13 ዞኖች ውስጥ ወካይ የሆኑ 12 ወረዳዎች ውስጥ በተጠለሉ 27 ተፈናቃይ ዜጎች የተጠለሉባቸው የገጠርና የከተማ ቀበሌዎች በመስክ ምልከታና በውይይት መሰብሰቡ ተጠ ቁሟል።አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሚያዝያ  26/2011በዘላለም ግዛው ", "passage_id": "463c125f0425d83d12c187fe9a469dee" }, { "passage": "ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ በፓርላማ ተገኝተው ካቀረቧቸው ዋና ዋና የዓመቱ የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ ምርጫን ይመለከታል:: ዘንድሮ በሚካሄደው ምርጫ ያለፉት ምርጫዎች ግድፈት እንዳይደገም እርምት እንደሚወሰድ ፕሬዚዳንቷ አስታውቀዋል:: የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችም ያለፈው ግድፈት እንዳይደገም መንግሥት የያዘውን ቁርጠኛነት አድንቀው፣ ለትግበራው የበለጠ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ያመለክታሉ፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ\nፍትህ ፓርቲ /ኢዜማ/\nየሙያ ማህበራት ግንኙነት\nቋሚ ኮሚቴ አባል\nአቶ ወንድወሰን ተሾመ\nእንደሚሉት፣ በአንድ የመድብለ\nሥርዓት ውስጥ ትልቁና\nዋነኛው ጉዳይ ምርጫ ሲሆን፣ለዚህም የዴሞክራሲ ተቋማት ሚና ከፍተኛ ነው፡፡በቀደሙት ምርጫዎች የዴሞክራሲ ተቋማት ሚና ደካማ መሆን ለምርጫዎች መበላሸት አንድ ምክንያት በመሆን ይጠቀሳል፡፡ አቶ ወንድወሰን፣‹‹ ያለፈውን ግድፈት:: የማረሙ ሥራ የብዙዎችን ድጋፍ ይፈልጋል፣ፕሬዚዳንቷም ለባለድርሻ አካላት የቤት ሥራ ማስተላለፋቸውም ይበል ያሰኛል ብለዋል፡፡ ‹‹እኛ የሚመለከተንና ጥሪውን የሰማን ኃይሎች ራሳችንን ቆም ብለን መፈተሽ አለብን፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪውና የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያ ናት፡፡የፓርቲዎችም ጥያቄ ኢትዮጵያን መምራት ነው፣ ኢትዮጵያ ግን መኖር አለባት፡፡›› ሲሉም ያስገነዝባሉ:: እንደ እርሳቸው ገለፃ፣ያለፈውን\nግድፈት የማረም ሥራ\nመጀመር ያለበት ከመንግሥት\nነው:: እንደ አገሪቱ\nርዕሰ ብሄር ፕሬዚዳንቷ\nምርጫው ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊና\nግልፅ በሆነ መልኩ\nይካሄዳል ብለው በዚህ\nመልክ አቅጣጫ ለህዝብ\nማቅረባቸው አንድ እርምጃ\nወደፊት እንደ መሄድ\nይቆጠራል፡፡ ከምርጫው አኳያ\nመልካም ጅማሬዎች እየታዩ ቢሆንም፣ ይህን ወደ ተግባር የመለወጡ ሥራ የበለጠ መንቀሳቀስን ይጠይቃል፡፡ይህ ከሆነ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የምትገነባበትን ምዕራፍ ጀምራለች ብለው እንደሚያምኑም አቶ ተሾመ ተናግረዋል፡፡ ይህ ወቅት የዴሞክራሲ ሥርዓቱን ለማምጣት በኢትዮጵያ መልህቅ የሚጣልበት የአምስት ዓመት ጅማሬ ይሆናል ብለው እንደሚያምኑም ነው ያስታወቁት፡፡ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ፕሬዚዳንት ዶክተር አረጋዊ በርሄ ፣ ‹‹ከምርጫ ቦርድ ጋር ባደረግነው ተከታታይ ውይይት እንዲሻሻሉ የተስማማንባቸው 33 አንቀፆች ቢሻሻሉ መልካም ነው›› ይላሉ፡፡ እንዲሻሻሉ የተጠየቁት አንቀጾች የምርጫው ያለፉት ጊዜያት ግድፈት ናቸው ብለው እንደሚያምኑ ያመለክታሉ፡፡‹‹እነዚህ የሚሻሻሉ ከሆነ ምርጫው አግባብነት ያለው መስመር ይዟል ብለው እንደሚያምኑ፣ይህ ካልሆነ ግን አቅጣጫው ከንግግር የዘለለ እንደማይሆን ይናገራሉ:: ቦርዱ ይበልጥ መንቀሳቀስ እንዳለበት የሚናገሩት ዶክተር አረጋዊ፣130 የፖለቲካ ድርጅቶች ከሚገኙበት ምክር ቤት ጋር በመነጋገር ግድፈቶችን ማስተካከል እንደሚገባም ያስገነዝባሉ፡፡ የኦሮሞ ነጻነት ግምባር /ኦነግ/ ቃል አቀባይ አቶ ቶሌራ አደባ ‹‹ለቀድሞው ግድፈት ዋናው ተጠያቂ የምርጫ ቦርድ ገለልተኛ አለመሆን ነው፡፡›› ይላሉ፡፡ዴሞክራያዊ፣ ነፃ እና ገለልተኛ ምርጫ እንዲካሄድ ቦርዱ ገለልተኛ ሊሆን እንደሚገባም ያመለክታሉ፡፡አቶ ቶሌራ ፤ቦርዱ የበኩሉን ጥረት እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ መዋቅሩን እስከታች በማውረድ ካለፈው የተሻለ ይሰራል ብለው ተስፋ ጥለውበታል፡፡እንደ አቶ ቶሌራ\nገለጻ፣ድርጅታቸው ቀደም ሲልም\nጀምሮ ምርጫው ነፃና\nገለልተኛ እንዲሁም ፍትሃዊ\nሆኖ እንዲካሄድ ይፈልጋል፡፡በምርጫ\nስም ህዝብ እንደ\nከዚህ ቀደሙ መታለል\nየለበትም፡፡በየምርጫ ጣቢያዎቹ ምርጫውን\nየሚቆጣጠሩ አካላት እንደውም\nበፓርቲው የተመደቡ ማለትም\nየመንግሥት ደጋፊ የመሆኑ\nነገር መደገም የለበትም::\nበዚህ መልኩ መስራት\nያለፈውን ግድፈት ለማረም\nያስችላል የሚል እምነት\nአላቸው፡፡አዲስ ዘመን ጥቅምት 4/2012አስቴር ኤልያስ", "passage_id": "ba151bd5f0f1133aa793c302838f8f80" }, { "passage": "ስለ ኢትዮጵያ ማወቅ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ሰነዶችን ቢበረብር፣ መረጃዎችን ቢያገላብጥ፣ ወይም በይነ መረቦችን ቢያስስ ከተፈጥሮና ሰው መሰራሽ ሀብቶቿ መካከል አንዱ አትሌቲክስ መሆኑን ይገነዘባል። ኢትዮጵያ በዓለም ሕዝብ ዘንድ ከእውቅናም በላይ ከበሬታን እንድታገኝ ካደረጉ ጉዳዮች መካከል በኦሊምፒክ ማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቀ የመጀመሪያው ጥቁር አትሌት የአበበ ቢቂላ አገር መሆኗ ትልቅ ድርሻ አለው። መረጃዎች አበበ ቢቂላ በባዶ እግሩን ሮጦ ከማሸነፉም በላይ ከአራት ዓመታት በኋላም ከዓለም ክብረወሰን ጋር ድርብ ድል መቀዳጀቱን ሳያስታውሱ አያልፉም። ስፖርቱን፣ አሸናፊነቱንና ክብሩን ትውልድ እየተቀባበለ ለዘመናት ማኖሩም በወርቅ ቀለም የተጻፈ የታሪክ አካል ነው። አትሌቲክስ ለኢትዮጵያ በቻምፒዮናዎች እና የኦሊምፒክ መድረኮች ላይ በመም፣ በጎዳና ወይም በሀገር አቋራጭ ውድድር ሜዳሊያ የምታስመዘግብበት ዘርፍ ብቻም አይደለም። ከኩራትና የአንድነት ስሜት ምንጭነቱ ባሻገር ሀገር ትለማና ትበለጽግ ዘንድ የበኩሉን በማድረግ እየተረባረበ ነው። ብርቅየ አትሌቶች በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ፤ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት፣ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ፣ በአግሮ ኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽን፣ በአውቶሞቲቭና በመሳሰሉት ዘርፎች በመግባት ለወጣቱ የስራ እድል በመፍጠር ረገድ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። ስፖርቱ መዋዕለ ንዋዩን በማፍሰስ የድርሻውን ከመወጣት ባለፈም ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይም ቅድሚያና ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆኑም እሙን ነው። በተለያዩ ጊዜያት በፌዴሬሽኑ፣ በአትሌቶችና በሙያ ማህበራት በተናጠልና በቡድን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለማውሳትም፤ ከወቅታዊው የኮሮና ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተከናወነውን ስራ በምሳሌትነት ማንሳት ይቻላል። የገንዘብና የቁሳቁሰ ድጋፍ ከማድረግም ባለፈ በማዕድ ማጋራት ላይም ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት ችሏል። አሁንም መንግስት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታና የውሃ ሙሌት ላይ የያዘውን አቋም በጽኑ እንደሚደግፍ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ግንባታው እስኪጠናቀቅ ድረስም የአትሌቲክስ ቤተሰቡ ከመንግስትና ከህዝብ ጎን የሚቆም መሆኑንም በድረገጹ ባወጣው መግለጫ አስነብቧል። ለረጅም ዓመታት ሲጓተት የቆየው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሂደቱ እየተፋጠነና የውሃ ሙሌቱም በተያዘው\nክረምት  የሚጀመር መሆኑን መንግስት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ነው ፌዴሬሽኑ የድጋፍ መግለጫውን ያወጣው። በዚህም የፌዴሬሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች፣ አትሌቶች፣ የአትሌት ተወካዮችና አሰልጣኞች፣ የአትሌቲክስ ዳኞች እንዲሁም በስፖርት ቤተሰቡ በቁርጠኝነት እንደሚደግፍ ጠቁሟል። ፌዴሬሽኑ ከዚህ ቀደም ቦንድ በመግዛትና ድጋፍ በማሰባሰብ፣ ከዚሁ ጎን ለጎን የፌዴሬሽኑ አመራሮችና የአትሌቲክሱ ቤተሰብ በስፍራው በመገኘት ግንባታውን መመልከቱ ይታወሳል። ከ40ሺ በላይ ሯጮችን ያሳተፉ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮችን በማካሄድም የግድቡን ግንባታ የሚደግፉ አካላትን የማነቃቃት ስራም አከናውኗል። በቅርቡም ፌዴሬሽኑ ለሕዳሴው\nግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ\nጽህፈት ቤት የገንዘብ\nድጋፍ አበርክቷል። አባይና የህዳሴ ግድቡ ለአትሌቶችና የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንደማንኛውም\nየህብረተሰብ ክፍል የህልውና\nጥያቄ በመሆኑም በአካል በቦታው  በመገኘት፣ ለግንባታው በማስተባበር፣ አቅም የፈቀደውን የገንዘብ አስተዋጽኦ በማድረግ እንዲሁም በግልና በቡድን ለግንባታው የሚያግዙ የዲፕሎማሲ ስራዎችም በተጨማሪነት እየተሰሩ እንደሚገኙም በመግለጫው ተመልክተዋል። ይህ ሂደት የአንድ ወቅት ብቻ ባለመሆኑ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ድጋፉን አጠናክሮ በመቀጠል፤ ስራው እንደ ድል አድራጊ አትሌቶች በጽናትና በቁርጠኝነት እንደሚጠናቀቅም እምነት ተጥሎበታል። ፌዴሬሽኑ ከግድቡ ባሻገር የደም ልገሳና አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የችግኝ ተከላ በቅርቡ ለማካሄድም በዝግጅት\nላይ ይገኛል። በዓለምና\nሀገር አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ በሚገኘው\nየኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ\n(ኮቪድ 19) ምክንያት እየተከሰተ\nያለውን የደም እጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት የደም ልገሳ መርሃ ግብር በማዘጋጀት\nፌዴሬሽኑ ለስፖርቱ ቤተሰቦች\nጥሪ አድርጓል። በቀጣይ ሳምንት ሰኔ  16/2012 ዓም ከማለዳው ሶስት ሰዓት ጀምሮ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቢሮ ሰራተኞች፣ አንጋፋ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ የአትሌት ተወካይ ማናጀሮች፣ ሁሉም የአትሌቲክስ ማህበራት አመራሮች፣ የክለብ አመራሮች በአጠቃላይ የአትሌቲክሱ ቤተሰብ በፌዴሬሽኑ አስተባባሪነት የደም ልገሳውን ለማካሄድ ቀጠሮ ይዛል። ፌዴሬሽኑ ከኢትዮጵያ ደም ባንክ አገልግሎት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ታሪካዊና አገራዊ ጉዳይ ላይ ሁሉም የድርሻውን እንዲያበረክትም ጥሪውን አስተላልፏል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተመናመነ ያለውን የሀገሪቷን የደን ሽፋን እንዲያገግም ለማድረግም ከመንግስት ጎን በመቆም የአረንጓዴ አሻራን በችግኝ ተከላ ለማሳረፍም እቅድ ይዟል። የአትሌቶች የህይወት ምንጭ የሆኑትን የዛፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የትና መቼ እንደሚከናወን በቅርቡ እንደሚያሳውቅም ጠቁሟል።  አዲስ ዘመን ሰኔ10/2012ብርሃን ፈይሳ ", "passage_id": "d8d94b43638fd2e8af912cafe5230dad" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- በግለሰብ ቸልተኝነት ማህበረሰብን እና አገርን ለአደጋ የሚጥል አካሄድ እንዳይፈጸም ህግ የማስከበር ስርዓቱ ጠንከር ባለ መልኩ እንዲፈጸም\n ትእዛዝ መተላለፉን በሚኒስትሮች ምክር ቤት የኮሮና ቫይረስን (ኮቪድ 19) ለመከላከል የተቋቋመው ንዑስ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ \nምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ኮሚቴው እስካሁን በተወሰኑ ውሳኔዎችና አጠቃላይ\n ሁኔታ ዝርዝር የአፈጻጸም ግምገማዎችን ማካሄዱን፣ በግምገማው መሰረት ለወደፊቱ መደረግ ስለሚገባቸው ጉዳዮች አቅጣጫ ማስቀመጡን አስመልክተው፤ህግና ስርዓትን የማስከበሩ ሥራ ከማስተማር ጎን ለጎን ተጠናክሮ\n እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡\nምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህብረተሰቡ የህግ አስከባሪ አካላት ባልተመቹ ሁኔታዎች እየሰሩት ያለውን ሥራ መደገፍና መተባበር እንደሚገባ ጠቅሰው፤ አንዳንድ ለአደጋ የሚያጋልጡ ምልክቶች ስላሉ የሁሉንም አካላት ርብርብና የተቀናጀ ሥራ እንደሚያስፈልግ ኮሚቴው መመልከቱን አስረድተዋል፡፡ \nበንግድ ስርዓቱ የታዩ አንዳንድ መጥፎ ምልክቶችን ለማስተካከል የአሰራር ስርዓት መዘርጋቱን የጠቆሙት አቶ ደመቀ፤ ችግሩን ለመሻገር የህሊና እርቅ መፍጠር ይገባል እንጂ የተለየ ትርፍ ለማግኘት መሻትና መጓዝ ከዜግነትና ሰዋዊ ሚዛን ያወርዳል ብለዋል፡፡ \nበዓለም ደረጃ ያለው አስከፊና አሳሳቢ ደረጃ በርቀት የሚታይ ሳይሆን በአገራችን በደጃችን ደርሷል ያሉት አቶ ደመቀ፤ ‹‹በሞት ደረጃ ተጋላጭ ባንሆንም ዜጎች ተጠቂ ሆነዋል፤ያለምንም መዘናጋት ለከፋው ችግር መዘጋጀት ያስፈልጋልም ››ሲሉ ተናግረዋል፡፡ \nእንደ እርሳቸው ማብራሪያ፤ መረበሽና መጨነቅ አያስፈልግም፡፡ አሻግረን እየተመለከትን እንደማይደርስብን እያሰብን ከተዘናጋን የከፋ አደጋ ሊያጋጥም ይችላል፡፡ ሁሉም ዘማች ሆኖ ኃላፊነቱን ለመወጣት መረባረብ\n ይገባዋል ፡፡ የዓለም የጤና ድርጅት ያስቀመጣቸውን ህግጋቶች በመፈጸም አደጋውን መከላከል ያስፈልጋል፡፡ ሁሉም ኃላፊነቱን ከተወጣ አገርን ነጻ ማድረግ ይቻላል፡፡ በሌሎች አገሮች የታየው አደጋ እንዳይደርስ አስፈላጊውን ጥረት ማድረግ ተገቢ ነው፡፡ \nየመገበያያ ስፍራዎች አካላዊ ርቀትን ጠብቆ የመተግበሩ ሂደት መሻሻሎች ቢታይበትም አሁንም ከፍተኛ ትኩረት ሊደረግበት ይገባል ፡፡ የሃይማኖት ተቋማት የእምነቱን ስርዓት ተከትሎና ርቀትን ጠብቆ እንዲከናወን ከሃይማኖት አባቶች ጋር ምክክር በመደረጉ ዜጎችን መታደግ እንዲቻል ትኩረት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ኮሚቴው ወስኗል፡፡ \nበፌዴራል መንግሥትና በክልሎች መካከል የሚወሰዱ የመከላከል ስርዓቶች ግንኙነታቸውን ማጠናከር፣ ወጥና ተመጋጋቢ የሆነ የመከላከል ስርዓት እንዲዘረጋ ኮሚቴው መወሰኑን አቶ ደመቀ አመልክተዋል፡፡ \nየኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን 87 የበረራ ግንኙነቶችን ዘግቷል ያሉት አቶ ደመቀ፤ በእዚህ ላይ በመመስረት ከፍተኛ የጥንቃቄ ሥራዎች እንደሚከናወኑና ከተለያዩ አገሮች የሚገቡ ዜጎች ለቆይታ ወደ ተመደቡ ሆቴሎች የመውሰዱ ሥራ የበለጠ ሊጠናከር እንደሚገባው ኮሚቴው ውሳኔ ላይ መድረሱንም ተናግረዋል፡፡\n እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ ፤ወረርሽኙ የጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና አጠቃላይ የአገር ህልውና እየሆነ መጥቷል፡፡ ከህብረተሰቡ የአኗኗር ሁኔታና ድህነት በመነሳት አስቀድሞ መዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ የኢኮኖሚ ጉዳትን ለመቀነስና አቅም ለመገንባት፣ በህብረተሰቡ በኩል ለመደጋገፍና ለመተጋገዝ ያለውን ፍላጎት በተቀናጀና ወጥ በሆነ ስርዓት እንዲመራ ኮሚቴው ወስኗል፡፡ የገቢ ማሰባሰብና የምግብ ክምችት ሥርዓትም ተዘርግቷል፡፡ \nእንደእርሳቸው ማብራሪያ፤ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ያሉ ዜጎች ካላቸው በማካፈል ያለውን ችግር ለመሻገር ያሳዩት ቁርጠኝነት የሚያበረታታ ነው፡፡ የሃብት አሰባሰብና አጠቃቀሙ በኃላፊነትና በጥንቃቄ ለቁርጥና ለባሰ ጊዜ እንዲውል ሥርዓቱን የበለጠ ማጠናከር ያስፈልጋል፡፡ መንግሥት ያቋቋመው የገቢ አካል እንጂ ሌሎች ጎን ለጎን የሚካሄዱ የገቢ ማሰባሰብ ሥራዎች ጠቀሜታቸው ያን ያህል ስለሆነ ወጥ በሆነው ሥርዓት ተመጋግቦ እንዲቀጥል ይደረጋል፡፡ \nበአገር ውስጥም ንብረታቸውን፣ የንግድ ድርጅታቸውን፣ መኖሪያ ቤታቸውን ሆቴላቸውንና ልዩ ልዩ አፓርትመንቶችን ለእዚህ ዘመቻ እንዲውሉ ለተወሰነ ጊዜ ያመቻቹ ዜጎች አሻራቸው በታሪክ የሚቀመጥ ነው፡፡ ሌሎችም ይህንን ተግባር ተከትለው አቅማቸው በፈቀደ\n መጠን ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ኮሚቴው አቅጣጫ አስቀምጧል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡ \nብዙ ዜጎች የዕለት ማደሪያ የሌላቸው መኖራቸውን በግምት ውስጥ ያስገባው ኮሚቴ፤ ለድርቅና ለተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች የተዘረጋውን የምግብ ክምችትን የማሳደግ ተግባር ኮሚቴው ተጠናክሮ እንዲተገበር ወስኗል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የገበያ ስርዓቱን በማሳለጥ የምግብ ክምችት አስተማማኝ ሆኖ መጥፎ ጊዜን ለመሻገር የሚያስችል አቅምን መገንባት ትኩረት እንደሚደረግበትም ጠቁመዋል፡፡ \nምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጸጥታ አካላት በጠረፍ ከጎረቤት አገሮች ጋር የሚያገናኙ መውጫና መግቢያ በሮችን እየለዩ አካባቢውን የመቆጣጠርና የመከላከል ሥራ እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ባልታሰበና ባልታቀደ ሁኔታ ከውጭ የሚገቡ ዜጎች መኖራቸውንና በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሥርዓትም ወደ ባሰ ችግር ለመጓዝ የሚሞክሩ እንዳሉ አስረድተዋል፡፡ \nበድንበር አካባቢ አመቺ የመቆያ ሥፍራዎች የማዘጋጀት፣ አስፈላጊ የኳራንቲንና የምርመራ ሥራዎች በመስራት ወደፊት ከህብረተሰቡ ጋር እንዲቀላቀሉ የማድረግ ሥራዎች እንዲተገበሩ መወሰኑንም አክለው ገልጸዋል፡፡አዲስ ዘመን መጋቢት 23/2012\nዘላለም ግዛው", "passage_id": "553f2f67234500e6518aa5bc5f089093" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የመስፋፋት ፍጥነት እና አገር ላይ ከሚያሳድረው ተጽእኖ አኳያ ዘገየ ካልተባለ በስተቀር አሁን መውጣቱ ተገቢ ነው ሲሉ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ፤ አደጋውን ለመቋቋምና ህዝብን ለማዳን ሊወሰዱ የሚገባቸው ዕርምጃዎች በሙሉ መወሰድ አለባቸው ብለዋል። ከወረርሽኙ መስፋፋት አኳያ የተለመደውን ማቆም ለጊዜው የግድ ይሆናል ብለዋል አቶ የሺዋስ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያስፈለገው ህብረተሰቡ ባግባቡ ትኩረት ባለመስጠቱ ሰው አደጋ ላይ ከመውደቁ አስቀድሞ ማዳንን ታሳቢ ማድረጉን ተናግረዋል። አሁንም መዘናጋቶች ይታያሉ የሚሉት አቶ የሺዋስ፤ የወረርሽኙ ፍጥነት ጊዜ ስለማይሰጥ መንግሥትና ብዙሃን መገናኛ የሚያደርጉት ጩኸት ህዝቡን በማንቃት መከላከል ላይ እንዲያተኩር ያደርገዋል ብለዋል። ህዝቡን አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ቀሪ ተግባራትን እየለዩ መረባረብ ይገባል ብለዋል። ህብረተሰቡ በየትኛውም ቦታ ርቀትን እንዲጠብቅ፣ በአብዛኛው በበሽታው የተያዙት ሰዎች ከአሜሪካ፣ ከዱባይና ከአውሮፓ የሚገቡ እንደመሆናቸው ጠንካራ ሥራ ሊሠራ እንደሚገባ አቶ የሺዋስ መክረዋል። ችግሩ ቢሰፋ ውጤቱ በጣም የከፋና አገር ላይ የሚያመጣውም ተጽእኖ ሊከብድ ስለሚችል፣ መጥፎ አሻራም እንዳይጥል አስቀድሞ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበትም ነው ያሳሰቡት። ወረርሽኙን በመከላከል በኩል ቀደም ሲል መንግሥት የተወሰኑ መዘናጋቶች እንደነበሩበት አንስተው፤ ባለፉት 10 ቀናት ጠንካራና ተከታታይ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰዋል። በከተማ አስተዳደሩ፣ በፌዴራልና በክልል ደረጃ የሚያስመሰግን እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም አክለዋል። በሃይማኖት አባቶችና በአገር ሽማግሌዎች እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴም ተስፋ ሰጪ መሆኑን ነው አቶ የሺዋስ የጠቆሙት። ወረርሽኙ ኢትዮጵያውያን በጋራ መኖር፣ ማምለክ፣ የትራንስፖርት አጠቃቀም፣ የመገበያያ ስፍራዎች ማህበራዊ ግንኙነቶች ህዝቦች ለዘመናት የኖሩበት እንደመሆኑ አሁን በተቃራኒ እንዲተገበር ሲደረግ ከባህል ጋር ሊያስቸግር እንደሚችል ጠቁመዋል። የኦፌኮ (ኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ ገብሩ ገብረማርያም፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በአገሪቱ አቅምና በህዝቡ የኑሮ ሁኔታ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ይገኛል ሲሉ ተግባሩን ያመሰግኑና፤ መታገዝ እንዳለበትም ተናግረዋል። የአገር ችግር በመሆኑ የፖለቲካ አቋም፣ አመለካከትና የሃሳብ ልዩነት ሳይደረግ ሁሉም ሊረባረብበት እንደሚገባም ይጠቅሳሉ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን ትክክለኛነት አቶ ገብሩ ያነሱና፤ በእዚህ አገር አቅም ማወጅ እንደሃጢያት ሊቆጠር አይገባም ብለዋል። ልዕለ ሃያሏ አገር አሜሪካም ማወጇን በማንሳትም፤ ለበሽታው ብቻ ሳይሆን ለጥፋት የተዘጋጀ ኃይል ሊኖር እንደሚችልም በስጋትነት ያነሳሉ። በመሆኑም መንግሥት የህዝብን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ስላለበት መታወጁ ተገቢ ነው ብለዋል። እንደእርሳቸው ማብራሪያ ንጽሕናን ለመጠበቅ የውሃ አቅርቦት በበቂ መልኩ መገኘት ይኖርበታል። ግን አንዳንድ አካባቢዎች ላይ እጥረት ይስተዋላል። ዓለም ባንክ አየር ጤና የሚባል ሰፈር ውሃ ከተቋረጠ ሦስት ሳምንት ሆኗል። በእዚህ ወቅት ይህ መሆኑ በጣም ያሳፍራል። አመራሮቹ በተሸከርካሪ እንዲያቀርቡ ጠይቄ አልተደረገም። በአንድ ተሽከርካሪ አምጥተው ህዝቡ ተረባርቦበታል። እንዲህ ዓይነት ግድፈቶች የመንግሥትን ጥረት ስለሚጎዱ መታረም አለባቸው ብለዋል። በመንግሥት አመራሮች ቅስቀሳ ብቻ ችግሩን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት ሊስተካከል ይገባል ብለዋል። ታዋቂ ሰዎች፣ የፖለቲካ አመራሮችና ሌሎች አካላት የሚሳተፉበት እንዲሆን ጠይቀዋል። ችግሩ ጥሎት የሚሄደው ጠባሳና ኢኮኖሚው ላይ የሚያስከትለው ተጽእኖ በቀላሉ ስለማይገመትም በሁሉም አካባቢዎች ችግሩ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ ጥረት እንዲደረግ አቶ ገብሩ ጠይቀዋል። አቶ በቀለ ገርባ በበኩላቸው፤ አስቸጋሪ ለሚሆንባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሰበሰበ ያለውን ሀብት ሕይወትን ለመታደጊያ እንዲውል ጠይቀዋል። በየከተሞች ሲሠሩ የነበሩ ወጣቶች ፋብሪካዎች በመዘጋታቸው ምክንያት ወደቤተሰቦቻቸው እንዲሄዱ ማድረግ በሽታውን የማዳረስ ያህል እንዳይሆን መጠንቀቅ ይገባል ብለዋል። ፋብሪካዎቹ ባይችሉ እንኳን ከመንግሥት ጋር ተባብረው የግማሽ ወር ደመወዝ በመክፈል እንዲቆዩ ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል። በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ የሚደረጉ በረራዎች እስከቅርብ ጊዜ ባለመቋረጣቸው በበሽታው የተጠቁት ሰዎች ከውጭ መግባታቸውን አቶ በቀለ ያስታውሱና፤ ቫይረሱ ተሰራጭቶ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት አንስተዋል። አሁንም አንዳንድ በረራዎች መቀጠላቸው ተገቢ ባለመሆኑ ውሳኔ ሊሰጥባቸው ይገባልም ብለዋል። እስከባለፈው ሳምንት መንግሥት በበርካታ ወረዳዎችና በትምህርት ቤቶች ጊቢ ብዙ ሰዎች ሲሄዱ እንደነበር በመጠቆምም፤ ሂደቱ ለበሽታው ስርጭት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚችል ግምት አለመወሰዱ ተገቢ እንዳልሆነም በመጥቀስ ተቃውመዋል። ታክስ ፎርስ መቋቋሙ በጎ መሆኑን በመጠቆምም፤ ለመከላከል ግን በቂ ዝግጁነትና ቆራጥነት የለም ብለዋል። አውቶቡሶችና ታክሲዎች እስከአሁን አገልግሎት መስጠታቸው ተገቢ እንዳልሆነም ነው የሚጠቅሱት። ሙሉ ለሙሉ ሥራ ለማቋረጥ ባይቻልም የግድ ወደሥራ መሄድ ያለባቸውን በእግር እንዲጓዙ አልያም ሌላ አማራጭ ሊፈለግላቸው ይገባል ብለዋል። ‹‹በህይወት መኖር አለብን መቋረጥ ግዴታ መሆን አለበት። ማትረፍ የሚቻለውን ሁሉ ማትረፍ አለብን›› በማለት ጠቁመው። ለህክምና ባለሙያዎች በቂ የመከላከያ ዕቃዎች ባልተሟሉበት ሁኔታ ራሳቸውን አጋልጠው ሰው ያክማሉ የሚል እምነት እንደሌላቸውም ተናግረዋል። አሁንም በሚያሳዝን ሁኔታ ሰዎች እየታሰሩ መሆናቸው ከመከላከሉ ጋር ይጋጫልም ብለዋል። ለሙያቸው የቆሙ በብቁ የህክምና ባለሙያዎች የተደራጀ የአማካሪ ኮሚቴ ማቋቋም አስፈላጊ መሆኑንም ጠቁመዋል። ኮሚቴው በዓለም አቀፍና በአገር ውስጥ ያሉ መረጃዎችን በማጠናከር ጠቅላይ ሚኒስትሩንና ታክስ ቡድኑን ማማከር ተልእኮ ይኖራዋል ብለዋል። በስሜታዊነት መድሃኒት ተገኝቷል በሚሉ ዓይነት የሚተላለፉ መረጃዎች ለስርጭቱ መስፋፋት ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጥር መጠንቀቅ እንደሚገባም መክረዋል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 5/ 2012 ዘላለም ግዛው", "passage_id": "57c931e8712c482f9656dbb9cc6b1ed8" } ]
6572de1e11f6beda2c812812083283c9
fc3f99ba8e0ba8fd5826f6b7d886bb24
ባለፉት 5 ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 33 ቢሊየን ዶላር ተገኝቷል ተባለ
መላኩ ኤሮሴአዲስ አበባ፡- ባለፉት 5 ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 44 ቢሊየን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 1 ነጥብ 33 ቢሊየን ዶላር መገኘቱን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ገለጹ። የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ባለፉት አምስት ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 44 ቢሊየን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 1 ነጥብ 33 ቢሊየን ዶላር ተገኝቷል። በዚህም ለማሳካት ከታቀደው 94ነጥብ3 በመቶ ማሳካት ተችሏል። የአምስት ወር አፈጻጸም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ224 ሚሊየን ብር ወይም የ20 በመቶ ብልጫ እንዳለው ያብራሩት ሚኒስትሩ፤ የህዳር ወር ብቻ ከታየም የ23 በመቶ ብልጫ የተመዘገበበት መሆኑን ገልጸዋል። የኮቪድ ወረርሽኝ በአለም ላይ ከፍተኛ ጫና ባሳደረበት እና እንደ ሃገርም ሰፊ የህግ ማስከበር ስራ እየተሰራ ባለበት ወቅት ይህ አፈፃፀም ከፍተኛ መሆኑንም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት። እንደ አቶ መላኩ ማብራሪያ፤ ባለፈው ዓመት ህዳር ወር ከወጪ ንግድ 191 ሚሊየን ዶላር የተገኘ ሲሆን በዚህኛው ዓመት በህዳር ወር ብቻ 232 ሚሊየን ዶላር ተገኝቷል። ይህም ከአምናው 43 ሚሊየን ዶላር ብልጫ አለው። ይህ ውጤት እንዲገኝ በማድረግ ረገድም የግብርናው ዘርፍ አጠቃላይ የወጪ ንግድ ወደ 62 በመቶ ሲሸፍን፤ ኢንዱስትሪ 12 በመቶ እንዲሁም ማዕድን ወደ 23 በመቶ እንደሚሸፍን ተናግረዋል። ባለፉት አምስት ወራት የግብርና የወጪ ንግድ ከእቅዱ 76 በመቶ ማሳካቱን ያብራሩት አቶ መላኩ፤የኢንዱስትሪ ውጤቶች ከእቅዱ 93 በመቶ እንዲሁም ማዕድን ከመቶ ፐርሰንት በላይ ማሳካት እንደተቻለ ተናግረዋል። እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፤ በፖሊሲ ደረጃ የተሰሩ ስራዎች እና እስከ ታች ድረስ ተቀናጅቶ መሰራቱ በወጪ ንግድ ዘርፍ ለተመዘገበው መልካም አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው። አሁን የተጀመረው ሰላም የማስከበር ሁኔታ፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ማሻሻያ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ሲገቡ ደግሞ የወጪ ንግድ ስራዎች ከዚህ የተሻለ ውጤት ሊያስመዘግቡ ይችላሉ። ሚኒስትሩ በመግለጫቸው፣ አነስተኛና መካከ ለኛ ኢንዱስትሪዎች አስፈላጊነት፣ በሀገራችን ኢንዱስትሪዎቹን እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች፣ ችግሮቹን ለመፍታት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች እንዲሁም መሰረታዊ ምርቶች አቅርቦትን ለማሻሻል የተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚህም የሀገሪቱ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የተቀናጀ ድጋፍ አላገኙም፤ መሬት የኤሌክትሪክና ሌሎች መሠረተ ልማቶች፣ የፋይናንስ አቅርቦት፣ የውጭ ምንዛሪ፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል፣ የገበያ ችግር ኢንዱስትሪዎችን እየተፈታተናቸው መሆኑን ተናግረዋል። እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ያብራሩት ሚኒስትሩ፤ የፋይናንስ አቅርቦት ችግሩን ከመፍታት አንጻር ለሊዝ ፋይናንስ 2ነጥብ2 ቢሊየን ብር፣ ለስራ ማስኬጃ 3ነጥብ2 ቢሊየን ብር፣ እንዲሁም ለፕሮጀክት ፋይናንስ 3ነጥብ2 ቢሊየን ብር በድምሩ 8ነጥብ6 ቢሊየን ብር መቅረቡን አስረድተዋል። በዚህም 1ሺ990 ኢንዱስትሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የኢንዱስትሪዎቹን የቅንጅት ችግሮችን ለመፍታትና በቂ ድጋፍ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ጋር ውይይት መደረጉን እና ከትናንት ጀምሮ እስከ ታህሳስ 20 ድረስ ከሁሉም ክልል የካቢኔ አባላት ጋር ቀደም ሲል በነበረው አፈፃፀምና ቀጣይ በሚኖረው ላይ ውይይት እንደሚደረግ አብራርተዋል። ለኢንዱስትሪዎቹ ቋሚ ድጋፍ የሚደረግበት የጋራ አሰራር መቀየሱን እና የግንዛቤ ፈጠራ ስራም በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። እንደ አቶ መላኩ ማብራሪያ፤ ተበዳሪዎች በበቂ ዕውቀት ስራቸውን እንዲሰሩ ከኢንስቲትዩቶች ጋር የተቀናጀ ስልጠና በመስጠት ሙያቸውን እያሻሻሉ እንዲሄዱ ይደረጋል። የአቅርቦት ችግርን መፍታት ሌላኛው ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ በመሆኑም፤ የመሳሪያና የግብዓት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ኢግልድና ኢትዮ-ኢንጂነሪንግ በአዲስ መልክ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37943
[ { "passage": "ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች ከአንድ ቢሊዮን 300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ፡፡ባሕር ዳር፡ ጥር 04/2013 ዓ.ም (አብመድ) ባለፉት ስድስት ወራት ወደ ውጪ ከተላኩ የተለያዩ ምርቶች ከአንድ ቢሊዮን 300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ የዘርፉን የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር በአዳማ ከተማ እየገመገመ ነው።የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋናው አረጋ በግምገማው መድረክ እንዳሉት ገቢው ከተገኘባቸው ምርቶች መካከል ወደ ውጭ የተላኩ ቡና፣ ቅመማ ቅመም፣ ጥራጥሬ፣ የቅባት እህሎች ይገኙበታል።ከማዕድንና ኢንዱስትሪ ምርቶች የተገኘው የውጪ ምንዛሬ የተሻለ መሆኑም ተገልጿል።የተገኘው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም ከ224 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር ብልጫ መገኘቱን አመልክተዋል።እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ የተሻለ አፈፃፀም ያለ ቢሆንም ሀገሪቱ ከውጪ ለምታስገባው የተለያዩ ምርቶች በዓመት ከ19 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ እያወጣች ነው። ሀገሪቱ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ምርቶች በዓመት የሚገኘው ከ3 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መዝለል አልቻለም ፤ አሁን ያለውን አቅምና አፈጻጸም ይዘን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ማሳካት አንችልም ብለዋል።በተለይም በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ተወዳዳሪ ለመሆንና የሀገሪቱን ጥቅም ለማስጠበቅ በወጭ ምርቶች ጥራትና ብዛት ላይ መስራት እንደሚገባ አምባሳደር ምስጋናው ተናግረዋል።የግብርናና ማኑፋክቸሪንግ የኢንዱስትሪ ምርቶችን የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ማሳለፍ፣ የንግድና ግብይት ሥርዓትን ማዘመን፣ የተቋማት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅም ማጎልበት፣ ድጋፍና ክትትል ላይ በሙሉ አቅም መስራት ግብ ለማሳካት እንደሚረዳ ጠቅሰዋል።በዚህም የመንግስትን እጅ መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ባለሃብቶች የሚያጋጥማቸውን ችግር በማቃለል በተለይም የአቅርቦት፣ መሬትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት መሰል መድረኮች ጠቃሚ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።", "passage_id": "d0cf5e0583326ac9689dc326c9272f78" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- የ2011 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የማኑፋክቸሪንግ የወጪ  ንግድ አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆኑን  የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ሽመልስ ሲሳይ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የ2011 ዓ.ም የሩብ ዓመት የማኑፋክቸሪንግ ወጪ ንግድ  ገቢ ታቅዶ የነበረው 180 ነጥብ ሦስት ሚሊዮን ዶላር ቢሆንም አፈጻጸሙ ግን 129 ነጥብ አንድ ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ ይህም አፈፃፀሙ 71 ነጥብ ስድስት በመቶ ያህል ነው፡፡ ይህ በ2010 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ተገኝቶ ከነበረው 119 ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ዶላር  ነው፡፡ ከዚህ ጋር ሲነፃፀር የዘንድሮው የ9 ነጥብ አምስት ሚሊዮን  ዶላር ብልጫ  ቢኖረውም የሚጠበቀውን ያህል ገቢ አለመገኘቱ ግን ሁኔታውን አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡እንደባለሙያው ገለጻ፣ የወጪ ንግዱ አፈፃፀም አነስተኛ እንዲሆን ምክንያት የሆኑት የአስተዳደር፣ ቴክኖሎጂ፣ የቴክኒክና አቅም ውስንነቶች መሻሻል አለማሳየት፣ የግብዓት አቅርቦት ጥራት በተሟላ መልኩ ማረጋገጥ አለመቻል እና የግብይት አቅም ውስንነቶች ናቸው፡፡ የገበያና ተያያዥ የዋጋ አፈፃፀም ችግሮች፣ የወጪ ንግድ ሥርዓትን አለማክበር እና የውጭ ምንዛሪ እጥረት አሁንም መፈታት ያልቻሉ ችግሮች መሆናቸውን  አስታውቀዋል፡፡በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ያለው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች አፈፃፀም መዘግየት  ከባለፉት ዓመታት ጀምሮ ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዋነኛ ማነቆዎች መሆናቸውን የጠቀሱት አቶ ሽመልስ  አሁንም ልዩ ትኩረት በመስጠት በዘላቂነት የሚፈቱበትን አቅጣጫ አስቀምጦ መረባረብን የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ የምታቀርባቸው የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ ሥጋና ወተት፣ ምግብና መጠጥ፣ ፋርማሲቲካል፣ ኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች፣ ብረታብረት፣ ኢንጂነሪንግ፣ ኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ ናቸው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 20/2011በሰላማዊት ንጉሴ", "passage_id": "fc2341fd6d263e622f047b688a369146" }, { "passage": "ባለፉት ሦስት ወራት ከወጪ ንግድ 640 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የንግድ ሚኒስቴር  አስታወቀ ።በሚኒስቴሩ የወጪ ንግድ ማስፋፊያ ዳይሬክተር ጀነራል የሆኑት አቶ አሰፋ ሙሉጌታ ለዋልታ እንደገለጹት በዘንድሮ የበጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 640 ነጥብ9 ሚሊዮን  ዶላር ገቢ የተገኘው የተለያዩ የግብርና፣ የማኑፋክቸሪንግና የማዕድን ምርቶች  ወደ  112  የዓለም አገራት  በመላክ ነው ።ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር አገሪቱ ከወጪ ንግድ ያገኘቺው ገቢ በ46 ሚሊዮን  የአሜሪካ ዶላር  መቀነሱን የጠቆሙት አቶ አሰፋ በተለይም የግብርናና የማዕድናት ምርቶች ከፍ ባለ መጠን ወደ ውጭ ቢላኩም በዓለም ገበያ የግብርናና የማዕድናት ዋጋ በመውረዱ ምክንያት ለገቢው መቀነስ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ ተናግረዋል ።በሩብ ዓመቱ ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች በተነጻጻሪነት ከቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ፣ቅመማቅመምና  የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች  ከዓምናው ተመሳሳይ ጊዜ የተሻለ ገቢ  ማስገኘታቸውን   አቶ  አሰፋ  አክለው ገልጸዋል ።እንደ አቶ አሰፋ  ማብራሪያ  ለወደፊቱ አገሪቷ ወደ ውጭ የምትልካቸውን የተለያዩ ምርቶች  ላይ እሴት በመጨመርናየምርት  ጥራት ላይ ማሻሻያ በማድረግ ይበልጥ ከምርቶቹ የሚገኘውን ገቢ  ማሳደግ ያስፈልጋል  ።ባለፉት ሦስት ወራት  የኢትዮጵያን ምርቶች  በመግዛት  ከፍተኛ የውጭ  ምንዛሪ  በማስገኘት  ሶማሊያ፣ ቻይና ፣ኔዘርላንድስ ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ እና ጀርመን  ከአንድ አስከ አምስት ያለውን ደረጃ  መያዛቸውን አቶ አሰፋ ተናግረዋል ።ኢትዮጵያ  በዘንድሮ የበጀት ዓመት ከወጪ ንግድ  4ነጥብ7 ቢሊዮን  የአሜሪካ ዶላር  ለማግኘት አቅዳለች ።   ", "passage_id": "8991b40b44e69cb2ac1b75b53088fda2" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥር 4 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የገቢዎች ሚኒስቴር በታህሳስ ወር 18 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን አስታወቀ።ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በወሩ 18 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ከእቅድ በላይ 18 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ገልጿል።አፈጻጸሙ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ22 ነጥብ 9 በመቶ ብልጫ ወይም የ2 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ልዩነት አሳይቷል ነው ያለው።በወሩ ከሃገር ውስጥ ገቢ 8 ነጥብ 59 ቢሊየን ብር እንዲሁም ከቀረጥና ግብር 9 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መሰብሰቡንም አስታውቋል።አፈፃፀሙ ጥሩ ቢሆንም በቅርንጫፎች መካከል ያለውን የአሰባሰብ ልዩነት በመቅረፍ የተሻለ ገቢ ለመሰብስብ መስራት ይገባል መባሉን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።", "passage_id": "5513df13dbf23fada40332524e925430" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2012  (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2012 በጀት ዓመት በ9 ወራት በግብርና ምርቶች ከ600 ሚሊየን  የአሜሪካን ዶላር በላይ የውጪ ምንዛሪ መገኘቱን ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ ÷ በበጀት ዓመቱ 9 ወራት 690ሺህ840 ቶን ምርት ለውጪ ገበያ በማቅረብ 818 ሚሊየን 611 ሺህ 770 ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 473 ሚሊየን 959 ሺህ 69 ቶን ምርት በመላክ 658 ሚሊየን 200 ሺህ 550 የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።በዚህም 255 ሺህ 340 ቶን የቅባት እህሎች በመላክ 339 ሚሊየን 718 ሺህ ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ከተላከው 162 ሺህ 782 ቶን ውስጥ 240 ሚሊየን 775 ሺህ 740 ዶላር የተገኘ ሲሆን ÷ ከተላኩት 367 ሺህ 189 ቶን የጥራጥሬ ሰብሎች ውስጥ ደግሞ 231 ሚሊየን 329 ሺህ 070 ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 249 ሺህ 637 ነጥብ 44 ቶን ተልኮ 154 ሚሊየን 663 ሺህ 650 ዶላር እንዲሁም 1 ሺህ 203 ቶን የተፈጥሮ ሙጫና እጣን በመላክ 4 ሚሊየን 164 ሺህ ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 977 ነጥብ 15 ቶን ተልኮ 4 ሚሊየን 204ሺህ6መቶ ዶላር ገቢ ተገኝቷል ነው የተባለው።በተመሳሳይ 46 ሺህ 232 ቶን ጫት በመላክ 240ሚሊየን 406ሺህ ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 44 ሺህ 930ነጥብ 26 ቶን ተልኮ 256 ሚሊየን0373ሺህ 10 ዶላር፣ 657 ቶን የብዕርና አገዳ እህሎች በመላክ 618000 የውጪ ምንዛሪ ለማግኘት ታቅዶ 927 ነጥብ 97 ቶን በመላክ 969 ሺህ 310 ዶላር የተገኘ ሲሆን ከባህር ዛፍ 2ሚሊየን 376 ሺህ 7መቶ የውጪ ምንዛሪ ለማግኘት ታቅዶ 1 ሚሊየን 549ሺህ930 ዶላር መገኘቱን ከኢንዱስትሪና ንግድ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።\nየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "25b111449184194e57e5eef41a213a23" } ]
2842a65a0dca6920e9f35de4c720888f
82db90507d2ac100827b203f9f318d6d
በሱዳን ካርቱም ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የኢትዮጵያ-ሱዳን የድንበር ጉዳዮች ከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት ተጠናቀቀ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ታህሳስ 13 እና 14 ቀን 2013 ዓ.ም በሱዳን-ካርቱም ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የኢትዮጵያ-ሱዳን የድንበር ጉዳዮች የከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት ትናንት ተጠናቀቀ፡፡በውይይቱ፣ ሁለቱ ወገኖች በጋራ የድንበር አካባቢ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሃሳቦችን የተለዋወጡ ሲሆን፤ ከጥቅምት ወር መጨረሻ ጀምሮ በጋራ ድንበር አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለውጦችና እንቅስቃሴዎች የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ እና መሬት ላይ ያለውን እውነታ የሚለውጡ በመሆናቸው በአስቸኳይ እንዲቆሙና ወደ ቀደመ ቦታቸው እንዲመለሱ ኢትዮጵያ አሳስባለች።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በገበሬዎች እና ባለሃብቶች ንብረት ላይ የደረሰ ከፍተኛ ጉዳት እና የዜጎች መፈናቀል ትኩረት እንደሚያሻው እና በአስቸኳይ መታረም ያለበት መሆኑን ኢትዮጵያ አሳስባለች።በተጨማሪም የሁለቱ አገሮች የጋራ ድንበር በተመለከተ ያሉ ማናቸውንም ዓይነት ልዩነቶች ሁሉንም በሚያስማማ መንገድ በውይይት ስለመፍታት እና የወደፊት አቅጣጫ ምን ይሁን በሚለው ዙሪያ መክረዋል።በኢትዮጵያ በኩል የድንበሩን ጉዳይ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ከቀደሙ ስምምነቶች ጋር በተጣጣመ መንገድ ከድንበሩ ጋር በተያያዘ የተቋቋሙና ስራቸውን ያላጠናቀቁ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎችን ስራቸውን እንደገና እንዲጀምሩ በማድረግ መፈታት እንዳለበት ተገልጿል። ይህም የሁለቱን አገራት ስትራቴጂካዊ እና ወንድማማቻዊ ግንኙነት እና የሁለቱን ሕዝቦች ዘላቂ ፍላጎትና ጥቅም የሚያስጠብቅ እንደሚሆን ተገልጿል።ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ ምክክራቸውን ለሁለቱ ወገኖች በሚመች ጊዜ በአዲስ አበባ ላይ ለማካሄድና ለመሪዎቻቸው የዚህኛውን ስብሰባ ሂደትና ውጤት ሪፖርት በማቅረብ በሚሰጣቸው አቅጣጫ መሰረት ምክክራቸውን ለመቀጠል በመስማማት ስብሰባውን አጠናቅቀዋል። በቀጣይ ስብሰባ በአካባቢው ያሉ ለውጦችን በመገምገም የድንበር ኮሚቴዎች ስራቸውን የሚቀጥሉበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክሩ ይጠበቃል።የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በክቡር የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ ሲሆን፤ ከሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ እና የሉዓላዊ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄኔራል ሞሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ ጋር ተገናኝተው ውይይት አድርገዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37982
[ { "passage": "የሱዳን መንግስት እና የዳርፉር ታጣቂ ቡድኖች የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ በሚያደርጉት ሂደት ወደ ጸጥታ ዝግጅቶች ከማምራታቸው በፊት የፓለቲካ ጉዳዮች ላይ በጁባ ውይይት አድርገዋል፡፡በዚህ ውይይትም የመንግስትና የታጣቂ ቡድኑ ተወካዮች የፍትህ ስርዓቱን በማሻጋገር ላይ እና በእርቅ በኩል ውጤት መመዝገቡን የሱዳን ነፃ አውጪ ግንባር ህብረት (ኤስ ኤል ኤፍ ኤ) ተደራዳሪ እና የሱዳን አብዮት ግንባር(ኤስ አር ኤፍ) ተደራዳሪ ኢብራሂም ዛሪባ  ተናግረዋል፡፡በዳርፉር የተፈፀመውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና የጦር ወንጀል የሚመረምር እና ክስ የሚመሰርት ልዩ የጦር ፍርድ ቤት መመስረትን ጨምሮ ለፍትህ ስርዓቱ እና ለተጠያቂነት አካሄዶችን ለማዘጋጀት ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተጠቁሟል፡፡የሱዳን ፍትህ እና እኩልነት ንቅናቄ ተደራዳሪ  አህመድ ቱጉድ በበኩላቸው በዚህ ድርድር በኦማር ሀሰን አልበሽር ዘመን በነበረው የህፃናት ውትድርና ፣ አስገድዶ መድፈር እና በጦር አዛዦች ለፈፀሙት ጥፋት ተጠያቂ አለመሆን በተመለከተ ውይይት እንደተደረገ ገልፀዋል፡፡ተደራዳሪው ሁሉም ወገኖች  በዳርፉር ምቹ ሁኔታን እና መረጋጋትን ለመፍጠር በሚስችሉ ዝግጅቶች ዙሪያ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን  ተናግረዋል፡፡ምንጭ፡- ሱዳንት ትሪቡን", "passage_id": "b57f41fc2d8ad06b5c8daae60a61bc53" }, { "passage": "በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና የሱዳን ግንኙነት እርስ በርሱ የተጋመደ በአብሮነትና በወንድማማችነት መሰረት ላይ የተገነባ በመሆኑ ከሰሞኑ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ የተከሰተው ችግር የሀገራቱን ወዳጅነትና ትስስር እንደማያሻክረው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ። አቶ ደመቀ መኮንን ሁለተኛው የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳዮች የከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት ጉባኤ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት፤ የኢትዮ ሱዳን የሁለትዮሽ ግንኙነት በአብሮነትና በወንድማማችነት መሰረት ላይ ለረጅም አመታት የተገነባ በመሆኑ ከሰሞኑ በድንበር ላይ የተፈጠረው ክስተት ከሁለቱ ህዝቦች ፍላጎት በተቃራኒው የሆነ ተግባር ነው። የሱዳን ወታደሮች በአካባቢው ላይ በወሰዱት እርምጃ የአርሶ አደሮች ምርት በእሳት ቃጠሎ ደርሶበታል፣ ከመኖሪያ ቦታቸውም ተፈናቅለዋል፤ ንጹሐን ዜጎች ሕይወታቸው አልፏል። በአዲስ አበባ በተደረገው ስብሰባ ላይ ውጤታማ ውይይቶች ተደርገው ከስምምነት መደረሱን ያስታወሱት አቶ ደመቀ፤ በድንበር አካባቢ ያለው የጸጥታና የሰላም ጉዳዮችን በጋራ ለመፍታትና የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ መልካም ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በቅርቡ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ የተከሰተው ችግርም የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች የሁለትዮሽ ግንኙነት እንደማያሻክረው ነው የገለጹት። እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ፤ ሱዳን ከዓለም አሸባሪነት መዝገብ ዝርዝር ውስጥ በአሜሪካ መንግስት በመሰረዟ ሱዳን ከአጋር ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላት ሲሆን፤ ይሄም የህዝቦቿን ልማት እና ዕድገት እውን ለማድረግ እገዛው የጎላ ይሆናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013", "passage_id": "a68fd598cb6283e863eb3601fc7f7dde" }, { "passage": "‹‹የሁለቱ አገሮች ግንኙነት በአስቸጋሪ ጊዜም ቢሆን ተጠናክሮ ይቀጥላል›› አብደላ ሐምዶክ፣ የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትርኢትዮጵያና ሱዳን በሚያዋስናቸው ድንበር ዙርያ ያሉ ግጭቶችንና የይገባኛል ጥያቄዎችን፣ በጥናትና ሁሉን አሳታፊ በሆነ የወሰን ማካለል ለመፍታት መስማማታቸውን አስታወቁ።ከድንበር ጉዳዮች በተጨማሪ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና በሌሎች የሁለትዮሽ ጉዳዮች ለመተባበር ስምምነት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ሁለቱ አገሮች ወደዚህ ስምምነት የደረሱት በከፍተኛ ባለሥልጣኖቻቸው ከግንቦት 9 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ከመከሩ በኋላ ነው።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ለሪፖርተር በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፣ የሁለቱ አገሮች ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ባደረጉት ፖለቲካዊ ውይይት ሰላማቸውንና ነባር የሆነውን መልካም ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል።የፖለቲካ ውይይቱ አብሮ በመኖርና በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ የረዥም ጊዜ ግንኙነት በሚያጠናክር መንፈስ መካሄዱን የገለጸው የቃል አቀባይ ጸሕፈት ቤቱ፣ የሁለቱን አገሮች የድንበር ጉዳይ የሕዝቦችን አብሮነትና የግንኙነታቸውን ታሪካዊ ዳራ ግምት ውስጥ በማስገባት ለመፍታት መስማማታቸውን ገልጸዋል።የሱዳን መንግሥት በውይይቱ የተሳተፈው በአገሪቱ የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ኦማር በሽር ማኒስ የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት ልዑካን ቡድን ይዞ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ቡድን በውይይቱ ተሳትፏል።ውይይቱ ሰኞ ግንቦት 10 2012 ዓ.ም. ከተጠናቀቀ በኋላ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ሁለቱ አገሮች የወሰን ማካለል ጉዳይን በተመለከተ ባደረጉት ውይይት ወደ ተሻለ ደረጃ ሊያሻግር፣ እንዲሁም የአካባቢውን ሕዝቦች ዘላቂ ተጠቃሚነት ሊያረጋግጥ በሚችል መንገድ መፈታት እንዳለበት መግባባታቸውን ገልጸዋል።በዚህ መሠረት በወሰን አካባቢ የተረጋጋ ሰላም እንዲሰፍን ተገቢነት የሌላቸው እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ፣ ሁሉም አርሶ አደሮች ያለምንም ሥጋት ወደ ግብርና ሥራቸው እንዲመለሱ ማድረግ እንደሚገባ ኢትዮጵያ አቋሟን እንዳሳወቀችና በሱዳን በኩልም ተመሳሳይ አቋም መያዙን አቶ ደመቀ ገልጸዋል፡፡ድንበር ማካለልን አስመልክቶ በተካሄደው በዚህ ውይይት የማካለሉ አስፈላጊነት የማያከራክር ቢሆንም፣ ችካል የመትከል ጉዳይ ሳይሆን በጥንቃቄና በውይይት የሚፈጸም ተግባር እንደሆነ በሁለቱም ወገኖች መግባባት እንደ ተደረሰበት አቶ ደመቀ አስረድተዋል።‹‹ወሰን የማካለል ጉዳይ ታሪካዊ ዳራውን በጠበቀ፣ ወቅታዊ ሁኔታውን ባገናዘበ፣ ያገባኛል የሚሉ አካላት ሙሉ ተሳትፎ ባካተተና የሕዝባችንን ተጠቃሚነት ባረጋገጠ አግባብ የሚከወን ነው፤›› ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በዚህ መንፈስ በሁለቱ አገሮች መካከል መግባባት እንደተፈጠረ ገልጸዋል።ከዚሁ ጋር በተገናኘም በሁለቱ አገሮች አዋሳኝ አካባቢዎች በየጊዜው የሚያጋጥሙ የፀጥታና የደኅንነት ችግሮችን በተለይም ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ንግድ፣ ዜጎችን በማገት ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን በጋራ የመቆጣጠርና የዜጎች መብት እንዲከበር ማድረግ እንደሚገባ የመድረኩ ዋነኛ ትኩረት እንደነበረ፣ ችግሮቹንም በዘላቂነት ለመፍታት ስምምነት የተደረሰበት መሆኑን አመልክተዋል።የሱዳን ልዑክ ወደ አገሩ ከተመለሰ በኋላ ለአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ሪፖርት ማቅረቡ ታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ በትዊተር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ በሱዳንና በኢትዮጵያ መካከል የተደረገው ፖለቲካዊ ውይይት ስኬታማ እንደነበር ገልጸዋል።የሁለቱ አገሮች አዋሳኝ ድንበር ላይ ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ከተደረገው ውይይት በተጨማሪ፣ በታላቁ የህዳሴ ግድብና በሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ለመተባበር የተደረገና መግባባት የተገኘበት እንደነበር አመልክተዋል።‹‹ወይይቱ ስኬታማ እንደነበር በመስማቴ ደስተኛ ነኝ፡፡ እርግጠኛ ነኝ የሁለቱ አገሮች ታሪካዊ ወዳጅነት በአስቸጋሪ ጊዜም ተጠናክሮ ይቀጥላል፤›› ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ሁለቱ አገሮች ቀጣዩን ዙር ተመሳሳይ ውይይት በመጪው ሰኔ ወር 2012 ዓ.ም. በሱዳን ካርቱም ለማካሄድ ተስማምተዋል። ኢትዮጵያና ሱዳን ረዥም ኪሎ ሜትሮችን የሚያካልል ድንበር የሚዋሰኑ ቢሆንም፣ የድንበራቸው ሕጋዊ ወሰን አልተበጀም።በድንበር አለመካለል ምክንያት በድንበር አካባቢዎች የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በተደጋጋሚ ከመጋጨታቸውም በላይ፣ ሱዳን የኢትዮጵያን መሬት በኃይል ወስዳለች ተብሎ ከፍተኛ እሮሮ ይሰማል፡፡ በተለይም የቀድሞው የግብፅ ፕሬዝዳንት ላይ በአዲስ አበባ ከተማ የግድያ ሙከራ ከሱዳን በዘለቁ አሸባሪዎች ከተፈጸመ በኋላ፣ በሁለቱ አገሮች ወታደሮች መካከል ግልጽ ውጊያ ከ15 ዓመታት በፊት ተከስቶ እንደነበር ይታወሳል።", "passage_id": "d89efa2829b21b78735c6223b4a9849c" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥር 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ ድንበር ኮሚሽን በዛሬው ዕለት ተቀማጭነታቸው በሱዳን ለሆኑ ዲፕሎማቲክ ሚሽኖች፣ ቆንስላዎች እና የዓለምአቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ገለፃ አድርጓል።መድረኩ ላይ የተገኙት በሱዳን የኢ.ፌ.ድ.ሪ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው የድንበር ጉዳይ ባሉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እና የጋራ የድንበር መድረኮች አማካኝነት በሰላማዊ መንገድ መፈታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።በዚህ ረገድ ከዳግልሽ ተራራ በስተሰሜን ከሰፈራ እና ከእርሻ መሬት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ እንዲመጣ የሚደነግገው እና በሁለቱ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በፈረንጆቹ ሐምሌ ወር 1972 የተደረገው የማስታወሻ ልውውጥ ከፍ ያለ ፋይዳ ያለው እንደሆነ በአጽንኦት አስረድተዋል።አያይዘውም በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ በተቀመጠው መሰረት የጉዊን መስመርን ዳግም ማካለል ከመጀመሩ በፊት ከዳግልሽ ተራራ በስተሰሜን ከእርሻ መሬት እና ሰፈራ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት የጋራ ልዩ ኮሚቴው ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ ያካተተ ሪፖርት ለጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቅረብ እንደሚኖርበት ገልጸዋል።ምንም እንኳ የጋራ ልዩ ኮሚቴው ሁለቱን ሀገሮች የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ ለማቅረብ ስምንት ዙር ስብሰባዎችን ቢያካሂድም ኃላፊነቱን ገና እንዳላጠናቀቀ ጠቁመዋል።በተጨማሪም አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ የኢትዮጵያ-ሱዳን ድንበር የጋራ ልዩ ኮሚቴ ስራ ባልተጠናቀቀበት ሁኔታ እና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥቅምት ወር መጨረሻ ህግ ለማስከበር ወደ ትግራይ ክልል ያደረገውን ስምሪት እንደ መልካም አጋጣሚ መጠቀሙን አንስተዋል።በዚህ መሰረት የሱዳን ሰራዊት ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ በመግባት ንብረት ከመዝረፉ፣ ወታደራዊ እና የእርሻ ካምፖችን ከማቃጠሉ ባሻገር በኢትዮጵያውያን ላይ እስራት፣ ጥቃት እና ግድያ መፈጸሙ እንዲሁም በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ማፈናቀሉን ጠቅሰዋል።ይኸውም የ1972 የማስታወሻ ልውውጥን በግልጽ የጣሰ ተግባር መሆኑን አስረድተዋል።አምባሳደሩ አክለውም በሁለቱ እህትማማች ሀገራት ጸንቶ ከቆየው አጋርነት እና ትብብር መንፈስ በተቃረነ መልኩ አጋጣሚውን በመጠቀም የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ሰራዊት ለቋቸው የወጣ ካምፖችን መቆጣጠሩን ገልጸዋል።አምባሳደሩ በተጨማሪም ሱዳን በችግር ውስጥ በነበረችበት ጊዜ ሁሉ ኢትዮጵያ ከሱዳን ህዝብ ጎን መቆሟን አውስተው፣ ኢትዮጵያ በውስጥ ጉዳይዋ በተጠመደችበት ወቅት ከሱዳን ሰራዊት የደረሰባት ጥቃት የሚገባት እንዳልነበረ መግለፃቸውን ከኤምባሲው ያገኘኘው መረጃ ያመለክታልአምባሳደሩ በገለጻቸው አክለውም የማስተካከያ እርምጃ በፍጥነት ካልተወሰደ፣ ታይቶ የማይታወቀው የሱዳን ሰራዊት ተግባር የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ብሎም የጋራ ድንበሩን ዳግም የማካለሉን ስራ የሚያወሳስብ እና ለሁለቱ ሀገራት ህዝቦች እንዲሁም ለቀጠናው ከፍ ያለ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚኖረው መሆኑን አንስተዋል።አምባሳደሩ የኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ልዩነቱን ሁለቱ ሀገራት በገቧቸው ስምምነቶች እና ባሉ የጋራ የድንበር መድረኮች መሰረት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ኢትዮጵያ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።አምባሳደሩ አክለውም ለችግሩ ዘላቂ እልባት ለመስጠት፡ አንደኛ፣ የሱዳን ሰራዊት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፈጸመውን ወረራ በመቀልበስ በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ በተቀመጠው መሰረት ወደ ቅድመ-ህዳር 2020 እንዲመለስ፣ሁለተኛ፣ ወደ ድንበር ዳግም ማካለል ከመገባቱ በፊት የጋራ ልዩ ኮሚቴው በ1972 የማስታወሻ ልውውጥ መሰረት ከዳግሊሽ ተራራ በስተሰሜን ከሰፈራ እና እርሻ መሬት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ የማቅረብ ስራውን እንዲያጠናቅቅ፣ሶስተኛ፣ የጋራ ድንበሩን ዳግም ለማካለል ሁለቱ ሀገራት ያቋቋሟቸው የጋራ የድንበር ኮሚሽን፣ የጋራ የቴክኒክ የድንበር ኮሚቴ፣ እና የጋራ ልዩ ኮሚቴ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እና ስራቸውን እንዲያጠናቅቁ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተዋል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን! ", "passage_id": "9660e485a92d6ef7070029e28872b1cf" }, { "passage": "በትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የተመራው የልዑካን ቡድን ከሱዳን መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ሚንስትር እንዲሁም ተጠሪ ከሆኑ መስሪያ ቤቶች ጋር የምክክር መድረክ አድርገዋል፡፡ምክክሩ በዋናነት ከዚህ ቀደም በአገራችን በኩል ፖርት ሱዳንን በመጠቀም ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችን  በጋራ በመፈተሽ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት በሚያስችሉ ተግባራት ዙሪያ ያተኮረ  ነው ተብሏል፡፡ፖርት ሱዳንን ተጨማሪ የወደብ አማራጭ በማድረግ የአገራችንን የወጪ-ገቢ ንግድ ለማሳለጥና ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ምርቶችን በዚሁ ወደብ በመጠቀም ለሰሜንና ምዕራቡ የአገራችን ክፍል ተደራሽ ለማድረግ በሚያስችሉ ሁኔታዎች ዙሪያ ጠቃሚ ውይይት መደረጉ ተገልጿል።በተጨማሪም  ሚኒስትሯ ከሱዳን ማዕድን እና ኢነርጂ ተጠባባቂ ሚኒስትር ኽይሪ አብዱልራህማን ጋር በማዕድንና ኢነርጂ ዘርፍ በተለይም በነዳጅ ምርቶች አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።ከሱዳን ወደ አገራችን የሚገቡ የነዳጅ ምርቶችን ከማጓጓዝ ጋር በተገናኘ እያጋጠሙ በሚገኙ ችግሮች እና  መፍትሄዎቻቸው እንዲሁም በሁለቱ አገራት ሊከናወኑ በሚችሉ የጋራ ፕሮጀክቶች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ከሱዳን ወደ አገራችን የሚገባውን የቤንዚን አቅርቦት ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጠናከር በሚረዱ የትብብር መስኮች ዙሪያም ውይይት መካሄዱን ከትራንስፖርት ሚኒስተር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።", "passage_id": "ea7caf12c0d1c9de64331ea452a21b9d" } ]
bf7e9fd86cc55225799972b38b5c0eed
b9b061b8a07fb2412bbd4d1b0da91348
ሚሊዮን ወልዴ ወደ አትሌቲክስ አሰልጣኝነት ገብቷል
ኢትዮጵያ ከፍተኛ ውጤት ባስመዘገበችበት የሲድኒ ኦሊምፒክ 5ሺ ሜትር ካሸነፈ በኋላ ደስታውን የገለፀበት የተለየ መንገድ በብዙዎች ዘንድ እስካሁንም እንዲታወስ ያደርገዋል፡፡ በወቅቱ ወጣት አትሌት የወርቅ ሜዳሊያ ማስመዝገቡ ከፍተኛ ደስታ የፈጠረ ቢሆንም በአትሌቲክስ ቤተሰቡ ዘንድ ተተኪ አትሌት መታየቱ ግን የተለየ ስሜት ያስገኘ ነበር፡፡ ነገር ግን ድንገት የታየው ተስፋ በቀጣይነቱ ሊገፋ አልቻለም፡፡ የያኔው ወጣት አትሌት ሚሊዮን ወልዴ ከሲድኒ ኦሊምፒክ ጣፋጭ ድሉ በኋላ በሌሎች ታላላቅ ውድድሮች ተጨማሪ ስኬት ያስመዘግባል ተብሎ እምነት ቢጣልበትም በውድድሮች ሳይታይ ቀርቷል፡፡ ውድድሩን እንዳጠናቀቀ ድሉን ያከበረበት መንገድ ከአብዛኛው ህዝብ የትዝታ ማህደር የማይደበዝዘውና እስካሁንም ለዓመታት መጥፋቱ የስፖርቱ ቤተሰብ ጥያቄ የሆነው የቀድሞው አትሌት ሚሊዮን ወልዴ ከጥቂት ዓመታት በፊት ለትምህርት ወደ አሜሪካን አገር እንደተጓዘ ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያ በጀግኖች አትሌቶቿ አራት የወርቅ፣ አንድ የብርና ሶስት የነሃስ በጥቅሉ በስምንት ሜዳሊያዎች ከምንጊዜውም የተሻለ ውጤት ባስመዘገበችበት የሲድኒ ኦሊምፒክ አንድ የወርቅ ሜዳሊያ እንዲመዘገብ ምክንያት የሆነው ሚሊዮን ለረጅም ጊዜ በትራክ እንዲሁም በተለያዩ ውድድሮች ባይታይም አሁን በባህር ማዶ ታዳጊዎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡ አትሌቱ በተለይ የታወቀው በሲድኒው ኦሊምፒክ ይሁን እንጂ በዓለም አቀፍ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው እአአ በ1998 ሲሆን፤ በተሳተፈበት ርቀት የዓለም ወጣቶች ቻምፒዮን ነበር፡፡ በቀጣዩ ዓመት ደግሞ በቤት ውስጥ ቻምፒዮና ሃገሩን በመወከል ከታላቁ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ጋር ተሳትፎ በ3ሺ ሜትር የነሃስ ተሸላሚ ሆኗል:: ራን ብሎግ ራን የተሰኘው ድረገጽ ከአትሌቱ ጋር በነበረው ቃለምልልስ አንጋፋው አትሌት በአሜሪካ በሚገኝ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የሃገር አቋራጭ አትሌት ተማሪዎችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡ ወደ አትሌቲክስ ስፖርት እንዴት እንደገባ የተጠየቀው ሚሊዮን ‹‹ልጅ እያለሁ ኳስ ነበር የምጫወተው፤ ለሌሎች ስፖርቶችም ፍላጎት ነበረኝ፡፡ እኔ ከጓደኞቼ ጋር ኳስ በምጫወትበት ሜዳ ላይም በርካታ አትሌቶች በየቀኑ ልምምድ ሲሰሩ እመለከት ነበር፤ ይህም ፍላጎት አሳድሮብኝ ወደ ስፖርቱ ልገባ ቻልኩ›› ሲል መነሻውን አስታውሷል፡፡ ፈጣን ሯጭነቱ ወደ አትሌትነት ለመሸጋገሩ ምክንያት ሲሆን፤ ወደ ክለብ ለመቀላቀልም የወሰደበት ጊዜ አጭር ነበር፡፡ የገባበት ክለብ በሃገሪቷ የተሻለ ከሚባሉት መካከል በመሆኑም በውድድር ተሳታፊ ለመሆን ረጅም ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ አሁን እያሰለጠነ በሚገኘው የሃገር አቋራጭ ውድድር ተሳታፊ የሆነው እአአ በ1996 የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ ታውን አስተናጋጅ የነበረችበት ውድድር ነው፡፡ በወቅቱ አሸናፊ በመሆኑ ከሃገሪቷ መሪ ኔልሰን ማንዴላ እጅ ሜዳሊያ የተበረከተለትን አጋጣሚም የማይዘነጋው ነው:: ሌላኛው የማይዘነጋና አስደሳቹ አጋጣሚ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያን ማጥለቅ ነው፡፡ ‹‹በህይወቴ ትልቅ ስፍራ ያለውም ነው፤ መንግስትን ጨምሮ ከበርካታ አካላትም ሽልማቶችን አግኝተናል›› በማለትም ሚሊዮን ያለፈውን ስኬት ያስታውሳል፡፡ በአሜሪካውያንና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መካከል ያሉትን ልዩነቶች እንዲጠቅስ የተጠየቀው ሚሊዮን የጎላ ልዩነት አለመኖሩን አንስቷል፡፡ ነገር ግን አሜሪካ በተሟላ የስልጠና ቁሳቁስና በሳይንሳዊ ስልጠና አትሌቶችን ስትደግፍ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ በተወሰነ መልኩ ለስልጠና አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁስን ብቻ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታ ላይ ልዩነት እንዳለ ያብራራል፡፡ ለወጣት አትሌቶች ስኬታማነት ልምዱን ያካፈለው አሰልጣኝ ሚሊዮን ወጣት አትሌቶች ለራሳቸው ግብ በማስቀመጥ ጠንክረው መስራትና ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ያስቀምጣል:: ይህንን የሚያደርጉ ከሆነም በብቃታቸው ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ያለውን እምነት ገልጿል፡፡ አዲስ ዘመን ጥር 6/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=25653
[ { "passage": "አትሌቲክስ ውድድሩ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ስታዲየም መካሄድ መጀመሩን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባወጣው መረጃ አስታውቋል።በዛሬው እለትም የአሎሎ ውርወራ ማጣሪያና ፍፃሜ፣ የስሉስ ዝላይ ማጣሪያና ፍፃሜ ውድድሮች እንደሚካሄዱ የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል።እንዲሁም ከ100 ሜትር እስከ 800 ሜትር የማጣሪያ ውድድሮች እንደሚካሄዱ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።", "passage_id": "ef0cac2523d80209c971130f6b564b5f" }, { "passage": "የዘንድሮው ዓመት የአትሌቲክስ አፍቃሪዎች ከዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ማግስት የታላቁን ስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ መዳረሻ በጉጉት የሚጠብቁበት በመሆኑ በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ የሚናፈቅ ነበር። የስፖርት ማህበራት የማጣሪያ ውድድሮችን በማካሄድ አገራትም ብሄራዊ ቡድኖቻቸውን በመመልመል ወደ ዝግጅት በመግባት ላይ እንደነበሩም ይታወሳል። ነገር ግን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ የዓለም ህዝብ ስጋት በመሆኑ ምክንያት ታላቁ ኦሊምፒክ ሊራዘም ችሏል። ከኦሊምፒኩ ጎን ለጎንም የበጋውን መግባት ተከትሎ በርካታ የግልና ዓለም አቀፍ ውድድሮችም የሚካሄዱበት ወቅት ቢሆንም በርካቶች በተመሳሳይ ምክንያት ተሰርዘዋል። \nኦሊምፒኩ ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሟል ይባል እንጂ ከሰሞኑ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ከዚያም በላይ ለሆነ ጊዜ ሊቆይ እንደሚችልና ከነጭራሹ የመሰረዝ እድል ሊገጥመው እንደሚችል ይጠቁማሉ። ምክንያቱ ደግሞ በመቶ ሺዎች የሚቆሩ ሰዎችን እየገደለ ያለው ወረርሽኝ ክትባት አሊያም መድሃኒት የሚያገኝለት የሕክምናው ዓለም ጠበብት እስካሁን ባለመኖሩ ነው። ይህም ለረጅም ጊዜ የተዘጋጁ አትሌቶችን ልፋት ገደል መክተቱ ሳይበቃ ተስፋ ለመቁረጥና ልምምድ ለማቆም እንዳያስገድዳቸው አስጊ ሆኗል። በአትሌቲክስ ስፖርት ውጤታማ በሆነችው ኢትዮጵያ በርካታ አትሌቶች የዚህ ችግር ተጋላጭ ሊሆኑ እንደሚችል ይገመታል። ያም ሆኖ አትሌቶች ይህን ክፉ ጊዜ በብልሃት ማለፍ እንዳለባቸው ይታመናል። \nበቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን ለመወከል ተመርጠው የነበሩ አትሌቶች በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ያሉበት ሁኔታ ምን ይመስላል፣ መራዘሙ ምን አስከተለባቸው፣ አትሌቶችና አሰልጣኞችስ ይህ ወቅት እስኪያልፍ ምን እያከናወኑ ይቆያሉ በሚሉ ጉዳዮች ላይ አዲስ ዘመን የበሄራዊ ቡድኑን አባላት አነጋግሯል። \nየቶኪዮ ኦሊምፒክ ተሳታፊ የሆኑ አትሌቶችና አሰልጣኞች ተመርጠው ወደ ሆቴል እንዲገቡ በማድረግ ሂደት ላይ ሳለ የመራዘሙ ዜና መሰማቱን የሚገልጹት የብሄራዊ ቡድኑ አስተባባሪና የረጅም ርቀት ዋና አሰልጣኝ ሱፐር ኢንቴንደንት ሁሴን ሸቦ ናቸው። መንግስት ባወጣው አቅጣጫ መሰረትም\n የቡድኑ አባላት በየቤታቸው ተበትነው እንዲቆዩ ተወስኗል። ይሁን እንጂ አትሌቶች በያሉበት ቦታ ሆነው በሳምንት ለአምስት ቀናት በግላቸው ቀላል እንቅስቃሴዎችን እንዲሰሩ እየተደረገ ነው። ቀድሞ ከሚሰሩት ለሁለት ቀናት እያረፉ 80 በመቶ የሚሆንና አቋምን ጠብቆ ለማቆየት የሚሰሩ እንቅስቃሴዎች ላይ እንዲያተኩሩ አሰልጣኞች አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ይህንንም አሰልጣኞችና አትሌቶች ቴሌግራምን በመሰለ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እንዲሁም በስልክ እየተወያዩ ተግባራዊ እንደሚያደርጉም አሰልጣኙ ይጠቁማሉ። \nየረጅም ርቀት ሩጫዎች ከትንፋሽ ጋር የተያያዘ እንደመሆኑ ከስልጠናው ጎን ለጎን በተለየ መልኩ የሚታይ ነው። በመሆኑም አትሌቶች ከሌላው ህብረተሰብ በተለየ ከ2 እስከ 5 ሜትር የሚሆን መጠን ርቀታቸውን መጠበቅ እንዳለባቸው ይታመናል። ከዚህ ባሻገር የመተጣጠፍ፣ የጂምናስቲክና ሌሎች የማሳሳቢያ እንቅስቃሴዎችን በሚያከናውኑበት ወቅትም የተስተካከለ የአየር ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጥ እንዳለባቸው የሚጠቁሙት ዋና አሰልጣኙ ናቸው። ከአካል ብቃቱ ባሻገር በአእምሮም ብቁ እንዲሆኑና እንዳይረበሹም አሰልጣኞች ያስገነዝባሉ።\nየውድድሩ መራዘም በአትሌቶች ዘንድ ምን ተፅዕኖ እንዳሳደረ የብሄራዊ ቡድኑ አባልና ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ተሞክሮውን ያጋራል። ኦሊምፒክ በአራት ዓመት አንዴ የሚመጣ ውድድር\n እንደመሆኑ ለአትሌቶች ትልቅ እድል የሚፈጥርና በጉጉት የሚጠበቅ ነው። በመሆኑም አትሌቶች እድሉን በመልካም ለመጠቀም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ እንደነበሩም ያስታውሳል። እርሱም ከግል አሰልጣኙ ጋር በመሆን ከአንድ ዓመት በፊት እቅድ በማውጣት ልምምድ የጀመረ ሲሆን፤ በጃፓን ጥሩ ውጤት የማስመዝገብ እቅድ ነበረው። የኦሊምፒኩ መራዘም እስኪሰማ ድረስም በመልካም ዝግጅት ላይ ቆይቷል። \nብሄራዊ ቡድኑ ከተበተነ በኋላም በግሉ ከውድድር ውጪ የሚሰሩ እንቅስቃሴዎችን ከማድረግ ወደኋላ አለማለቱን በዶሃ የዓለም ቻምፒዮና የ5 ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊው አትሌት ሰለሞን ይጠቁማል። ስልጠናውም ቀድሞ ከሚሸፍነው ርቀት ያነሰ የትንፋሽ፣ ጂምናስቲክና ሌሎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን እንደሚያጠቃልል ይናገራል። ይህንንም ከታናሽ ወንድሙ ጋር በመሆን ርቀታቸውን በጠበቀ መልኩ በቤትና ወደ ጫካ በመሄድ ያከናውናሉ። ከአሰልጣኞችም አትሌቶች በብቃታቸው እንዲቆዩ ለማድረግ በስልክና በሌሎች መንገዶች ግንኙነታቸውን እንደቀጠሉ ያብራራል። \nየኦሊምፒኩ መራዘም በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ በአዘጋጇ ጃፓን፣ በተሳታፊ አገራት እንዲሁም አትሌቶች ዘንድ ተጽእኖ ማሳደሩ ይታወቃል። በአንጻሩ የጠቀማቸውም አልጠፉም፤ እነርሱም በጉዳት ምክንያት ለኦሊምፒኩ ብቁ\n ያልነበሩ አትሌቶችን መሆናቸውን አሰልጣኝ ሁሴን ይጠቁማሉ። ከዚህ ባሻገር ወጣትና ተተኪ አትሌቶችን ለአንድና ከዚያ በላይ ላለ ዓመት መራዘሙ የሚጠቅማቸውና ወደ ተወዳዳሪነት እንዲመጡ እድል የሚሰጥ እንደሚሆንም እምነት አላቸው። ምናልባትም ስጋት ሊሆን የሚችለው በጥሩ ብቃት ላይ ለሚገኙ ኤሊት አትሌቶች ሲሆን፤ ምክንያቱ ደግሞ በአንድ ዓመት ልዩነት ሊከሰት የሚችለውን የአቋም መውረድ ወይም ጉዳት ማስተናገድ ለመገመት አዳጋች በመሆኑ ነው። በጥቅሉ ሲታይም መዋዕለ ነዋይ ላፈሰሱ አገራትና በእቅድ ሲንቀሳቀሱ ለቆዩ አሰልጣኞችና ስፖርተኞች እንዲሁም ሌሎች አካላት ጉዳቱ በቀላሉ የሚገመት እንዳልሆነ ያስቀምጣሉ። በመሆኑም ይህ ለዓለም ስፖርት ከፍተኛ ኪሳራ የሚያስከትል መሆኑን ይናገራሉ። \nበኦሊምፒክ ለትልቅ ውጤት ከሚጠበቁት አትሌቶች መካከል አንዱ የሆነው ሰለሞንና ሌሎች የቡድን አጋሮቹ በጥሩ አቋም ላይ እያሉ ውድድሩ በመራዘሙ ደስተኛ እንዳልሆነ ወጣቱ አትሌት ይናገራል። ምክንያቱ ደግሞ አሁን ያለበትን ብቃት በቀጣዩ ዓመት ላያገኘው ስለሚችል ነው። ነገር ግን ቀዳሚው የሰው ልጅ ህይወት በመሆኑ ደስተኛም ባይሆን ከሁኔታዎች ጋር ራሱን ለማስማማት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ሌሎች አትሌቶችም ከክለብ የተበተኑ በመሆኑ በተለያዩ ስፍራዎች ይገኛሉ። በዚህ ምክንያትም ልምምድ ከማቋረጥ ይልቅ ከአቋማቸው እንዳይወርዱ ጥንቃቄ እያደረጉ ባሉበት ሆነው ዝግጅታቸውን ቢቀጥሉ መልካም እንደሆነ ምክረሃሳቡን ያጋራል። በክፍለ አገር የሚገኙ ባልደረቦቹም የሚያገኙትን መረጃ ለሌሎችም እንዲያጋሩ መክሯል። \nአሰልጣኙ በበኩላቸው ለአትሌቶች ‹‹ከህይወት በላይ ምንም የለም፤ የትኛውም ነገር ይደረስበታል። በመሆኑም መንግስትና የጤና ሚኒስትር የሚያወጧቸውን መመሪያዎችና አቅጣጫዎች መከተል አስፈላጊ መሆኑን ያስታውሳሉ። እጅን መታጠብ፣ ርቀትን መጠበቅ፣ በሰዎች መካከል ሲገኙ አፍና አፍንጫን መሸፈን እና የህመም ምልክቶች ሲሰሟቸው ለጤና ባለሙያዎች በፍጥነት ማሳወቅ አለባቸው›› ሲሉም ያስገነዝባሉ። ከአትሌቶች ወጪ ያሉ ዜጎችም ይህ ወቅት እስኪያልፍ ግንኙነታቸውን ከቀድሞው እንዲቀንሱና በመንግስት የተቀመጠውን አቅጣጫ ያለመወላወል ተግባራዊ እንዲያደርጉም ጥሪያቸውን ያቀርባሉ።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 26/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "27dde6a31e62972ae266112506eedf87" }, { "passage": "ይህ በአለም የኢትዮጵያን ስም ያስጠራ አትሌት ታሞ አልጋ ከያዘ ሁለት አመታት ሊያስቆጥር ነው። ሁለቱም ሳምባዎቹ ከፍተኛ ህክምናን ይሻሉ። ህክምናውን ካናዳ ቶሮንቶ ሆስፒታል ውስጥ በመከታተል ላይ ይገኛል። ከትላንት በስትያ ህይወቱ እንዳለፈ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ተገልፆ ነበር። ሻምባል ምሩፅ ይፍጠር ህይወቱ አላለፈም፤ በተሻለ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ባለቤቱ ወ/ሮ ርሻን ስልክ ላይ በመደወል አረጋግጠናል። ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ያድምጡ። ", "passage_id": "98de2b5f61e41fca4d629164a9f255d4" }, { "passage": "በሪዮ ኦሊምፒክ በወንዶች ማራቶን ሁለተኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ከኦሊምፒክ ቡድኑ ጋር ሳይመለስ ቀርቷል፡፡አትሌቱ ባለፈው እሑድ በሪዮ ኦሊምፒክ የመዝጊያ ውድድር የተካሄደውን የማራቶን ሩጫ ሊያጠናቅቅ ሲል በኦሮሚያ ክልል ለሚካሄደው የተቃውሞ ድጋፍ እጆቹን ከጭንቅላቱ በላይ በማጣመር ተቃውሞውን በኦሎምፒክ መድረክ ላይ ከገለጸ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ፣ ‹‹እኔ የኦሮሞ ተወላጅ ነኝ፡፡ ቤተሰቦቼ በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ ስለዲሞክራሲያዊ መብታቸው ካወሩም ይገደላሉ፤›› ብሏል፡፡ አትሌቱ ይህንን ተቃውሞ በማድረጉ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ ሊታሰር ወይም ሊገደል እንደሚችል ተናግሯል፡፡ሆኖም የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፣ ለአገሩ የብር ሜዳሊያ ያስገኘው ይህ አትሌት በፖለቲካ አቋሙ ምክንያት የሚደርስበት ነገር አይኖርም፡፡ ምንም እንኳን አቶ ጌታቸው አትሌቱ ወደ አገሩ ሲመለስ ከሌሎቹ የኦሊምፒክ ቡድኑ አባላት ጋር ጥሩ አቀባበል ይደረግለታል ቢሉም፣ አትሌት ፈይሳ ከኦሊምፒክ ቡድኑ ጋር ሳይመለስ ቀርቷል፡፡የ26 ዓመቱ አትሌት ፈይሳ ያለው እዚያው ብራዚል ውስጥ ሲሆን፣ አትሌቱን ለመርዳት ሦስት ሰዎች ሪዮ መግባታቸውንና 91 ሺሕ ዶላር መሰብሰቡን አስተባባሪዎቹ ለአሜሪካን ድምፅ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡በሪዮ ኦሊምፒክ አንድ የወርቅ፣ ሁለት የብርና ሦስት የነሐስ ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከዓለም 44ኛ ከአፍሪካ ደግሞ ሦስተኛ ደረጃ በመያዝ ዝቅተኛ ውጤት ያስመዘገበው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ልዑክ፣ ማክሰኞ ነሐሴ 17 ቀን 2008 ዓ.ም. ከምሽቱ 3፡30 ሰዓት አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ለኦሊምፒክ ልዑካኑ አቀባበል ያደረጉት የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን ሑሴን ናቸው፡፡ ለኦሊምፒክ ቡድኑ የተደረገው አቀባበል እጅግ የተቀዛቀዘ ሲሆን፣ በአቀባበሉ ላይም በብዛት ጋዜጠኞችና የአየር መንገዱ ሠራተኞች ነበሩ የተገኙት፡፡  ", "passage_id": "9b4d9168d139fb51798a98a9fa8b3307" }, { "passage": "ከትላንት በስቲያ እሁድ እለት በተደረገው በዚህ የቤት ውስጥ ውድድር 3፡47፡01 በመግባት ሪከርዱን አሻሽሏል። \n\nበዚህ ውድድር ላይ አሜሪካዊው ጆኒ ግሬጎሬክ 3፡49፡98 በመግባት በሁለተኛነት አጠናቋል። \n\n•\"ሥልጣን ለደም ግፊት አጋልጦኛል\" ኃይሌ ገብረሥላሴ \n\n\"ሪከርድ መስበር በጣም ደስ ይላል፤ አንድ ሰው የሚሮጠው የሆነ ነገር ለማግኘት ነው።\" የሚለው አትሌቱ ለሯጭም ከፍተኛ ደረጃ እንደሆነ ይናገራል። \n\n\"አንድ አትሌት በህይወቱ የሚያስደስተው ነገር ኦሎምፒክ ማሸነፍና የአለም ሪከርድ መስበር ነው። ስለዚህ በጣም ደስ ብሎኛል።\" በማለት ለቢቢሲ ገልጿል።\n\n•አልማዝ እና ፋራህ ከመጨረሻ ተፋላሚዎች መካከል ናቸው\n\nሪከርድ በመስበሩ የሚያገኘው ገንዘብ ምን ያህል እንደሆነ ከቢቢሲ ለቀረበለት ጥያቄም ከዚህ ቀደም ሪከርድ የሚሰብር የሚያገኘውን ያህል እንደሆነ ተናግሯል። \n\nበአልግሩሽ ተይዞ የነበረውን ሬከርድ በአንድ ደቂቃ በአርባ አራት ሰከንዶች ያሻሻለው ዮሚፍ በሶስተኛው ሙከራ ሪከርድ መስበር እንደቻለም ተዘግቧል። \n\n•ኤኤንሲ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑን ውሳኔ 'ዘረኛ' ነው አለ\n\nየ21 አመቱ ዮሚፍ ከሶስት ሳምንታት በፊት ኒውዮርክ ውስጥ በተመሳሳይ ርቀት ውድድር ያደረገ ሲሆን፤ በወቅቱም በ0.01 ሴንቲ ሰከንድ ምክንያት ሪከርዱን ሳይሰብር ቀርቷል። \n\nበወቅቱ ስለነበረው ስሜትም አትሌቱ ለቢቢሲ ተናግሯል \" ያኔ በጣም ተሰምቶኝ ነበር፤ ውድድሩን ስጨርስ ዝቅ ብየ ቢሆን ኖሮ ሪከርዱን እሰብረው ነበር።\" የሚለው አትሌቱ በቀጣይነትም ረጅምና መካከለኛ ርቀት የመሮጥ እቅድ እንዳለው ተናግሯል። \n\n\"ትልቁ ሀሳቤ ከቤት ውጭ በአምስት ሺ ሜትር ሪከርድ መስበር ወይም ፈጣን ሰአት ማስመዝገብ እፈልጋለሁ\" ብሏል። \n\nዮሚፍ ያስመዘገበው ሰአት በኢትዮጵያም ውስጥ ፈጣኑ ሲሆን ይህም በአማን ወቴ 3፡48፡60 ተይዞ የነበረውን አሻሽሎታል ማለት ነው።\n\n ", "passage_id": "ace6a2ceb9ee2e8fd5212b5e4c40059d" } ]
c90a83f56698889e148828359bcbc76b
9c318ce05c97dcd4dd8c608b7a1fd4f8
የሕግ የበላይነት ባለመከበሩ፣ እንደ አገር ከተመዘገቡት ድሎች ያመለጡት ዕድሎች በእጅጉ የበዙ መሆናቸው ተገለፀ
ዋቅሹም ፍቃዱአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች፣ ህዝቦቿም በአንድም በሌላ በደም የተሳሰሩ ቢሆንም ሁሉንም በእኩል የሚዳኝ፣ የአገር ልማትና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ህግ ተግባራዊ ባለመደረጉ ምክንያት ባለፉት ዓመታት እንደ አገር ከተመዘገቡ ውጤቶች፣ ያመለጡ በረከቶች በእጅጉ እንደሚያመዝኑ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ገለጹ፡፡ኮሚሽነሩ፣ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት አስተያየት፤ አገራችን በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች በመሆኗ በቀላሉ ሰርተው የሚለወጡባት፣ አየሯ ተስማሚና ለኑሮ የምትመች ናት፡፡ ይሁን እንጂ በከፋፋይ አስተሳሰብ የተቃኘና ከአገር ይልቅ የቡድኖች ህግ ለዘመናት ገዝፎ በመቆየቱ ለሌላ መትረፍ የምትችል አገር በምግብ እንኳ ራሷን መቻል አቅቷት ለውጭ እርዳታ እጇን ስትዘረጋ ቆይታለች፡፡ ዛሬም ከውጭ እርዳታ ባለመላቀቋ እና የዚህ ምክንያቱም ተፈጥሯዊ ሳይሆን ሰው ሰራሽ እንደመሆኑ ሁሉም ዜጋ በቀጣይ በኢትዮጵያ እድል ላይ አስቦና ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል።እንደ ኮሚሽነር አበረ ገለጻ፤ ህግና ልማት የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። ያለፉት ታሪኮች አገርና ህዝብ ባልተስተካከለ ሚዛን የሚመራ ህግ ተግባራዊ ባለመደረጉ ምክንያት ኢትዮጵያ አስከፊ ብጥብጥና ውድመት ለማስተናድ ተገዳለች። ይህ ደግሞ አገሪቱን አቅም አሳጥቶ፣ አመት ሙሉ ምርት ማምረት የሚያስችሉ ወንዞችና ለም አፈር እያላት የስንዴ ለማኝ ሆናለች።ወደ ዘመነ መሳፍንትና ከዚያ በፊት ያሉ ዘመናት በታሪክ ሲቃኙ የኢትዮጵያ ህዝቦች ከዳር ወደ መሀል አገር እንዲሁም ከመሀሉ ወደ ዳር በተደረገው እንቅስቃሴ በጋብቻ ያልተሳሰረና ያልተዋለደ እንደሌለ የሚናገሩት ኮሚሽነሩ፤ ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ ግን ጎጠኝነት በመንሰራፋቱ ምክንያት በደም መተሳሰራችን ተረስቶ፣ የህግ የበላይነትም ጠፍቶ፣ ይልቁንስ ህግ በአገር እይታ ሳይሆን በቡድን እይታ የሚተረጎምበትና የሚተገበርበት ዘመናት እንደ ነበሩ ያስረዳሉ።በቡድን የሚቃኝና የሚዳኝ ህግ ለአገር ዕድገት ትልቅ ማነቆ ስለሆነ፣ ለአገር እድገት ከታሰበ ህግ ለሁሉም ክፍት መሆን እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፤ ህግ ከአገርና ከህዝብ ፍላጎት አንጻር እየተሻሻለ የሚሄድ እንጂ ከቡድን ፍላጎት አኳያ የሚሻሻል ወይም የሚተው አለመሆኑን ገልጸዋል። የቡድን ህግ ደግሞ በባህሪው ቡድኑን የሚጠቅምና የሌላውን የሚጎዳ በመሆኑ አገራችንን ምን ያህል ዋጋ እንዳስከፈላት ባለፉት 27 ዓመታትን ማየት ብቻ በቂ እንደሆነ ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ ህግና ህገ መንግስታዊ ስርዓት ተግባራዊ እንዲሆን እንዲሁም የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ፣ በመጀመሪያ ደረጃ ሰው ህግን እንደ ቡድን ወይም እንደ ብሔር ሳይሆን እንደሰው በሳይንሳዊ ዘዴ ማሰብ አለበት። ካልሆነ የአገር ህልውናና የህዝቦች አብረው የመኖር ዋስትና አደጋ ላይ ይወድቃል። ሲቀጥል፣ የፍትህ ተቋማት በሙያዊ ስነ ምግባርን በተላበሰ መልኩ ያለምንም አድሎ ህዝብና አገር በቅንነትና በፍጹም ቁርጠኝነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋል። ህዝብም እንደ ህዝብ ህግን አውቆ ለመብቱ ዘብ የመቆም፣ ግዴታውን በአግባቡ የሚወጣ መሆን አለበት። ከሁሉም በላይ ደግሞ መንግስት ለህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ግንባር ቀደም ሚና መጫወት ይጠበቅበታል።ለላቀ የአገር ልማት እና አንድነት ያገኘነው መልካም ውጤቶች በአግባቡ ለመያዝ እንዲሁም ያመለጡን ዕድሎች እጃችን ለማስገባት የህግ የበላይነት መከበር ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነር አበረ፤ ሳይንሳዊ የህግ ምክሮችና የልማት ጉዳዮችን አስመልክተው በመጽሐፉ ያሰፈሩት ሀሳቦች በተቻለ መጠን በተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ህዝቡ ጋር እንዲደርስ ጥረት በማድረግ፣ አገራችን የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ እንደሚሰሩ አሳውቀዋል።ኮሚሽነሩ፣ ጊዜያዊ ችግሮች ላይ ከመጠመድ ይልቅ ዘላቂ መፍትሔ ላይ በማተኮር ያደጉ አገሮች የተከተሉት የህግ ሳይንስ በአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስተሳሰር “የህግ የበላይነት ለሀገራዊ ልማት” በሚል ርዕስ የጻፉት መጽሐፍ ለአንባቢያን እንደበቃም ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37981
[ { "passage": "በሕገ መንግሥቱ የተከበሩ መብቶች በማንኛውም ሁኔታ ሲጣሱ፣ ከሕገ መንግሥቱ ድንጋጌ አኳያ ለመተርጎምና ለማስከበር የሕገ መንግሥት ፍርድ ቤት መቋቋም እንዳበት ምሁራን ሐሳብ አቀረቡ፡፡ሐሳቡን ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ምሁራን፣ በጥብቅናና በተለያዩ ቦታዎች የሕግ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ‹‹የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት አተረጓጎም ሥርዓት መሻሻል ያስፈልገዋል?›› በሚል ርዕስ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ታኅሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሄደው የግማሽ ቀን ዓውደ ጥናት ላይ የተገኙ ምሁራን እንደገለጹት፣ በሕገ መንግሥቱ የተከበረ መብት በማንኛውም ሁኔታ መከበር አለበት፡፡ ነገር ግን ሕገ መንግሥትን የሚጥሱና ኢሕገ መንግሥት የሆኑ አዋጆችና ውሳኔዎች ሲወጡና ሲሰጡ መቆየታቸውንና እስካሁንም እንዳልታረሙ አስረድተዋል፡፡በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ጌታቸው አሰፋ (ዶ/ር) በዓውደ ጥናቱ ላይ እንደተናገሩት፣ በእሳቸው እምነት የሕገ መንግሥት ትርጉም ሥርዓት መሻሻል አለበት፡፡ የሕገ መንግሥት ትርጉሞችም ሦስት ዓይነት መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የመጀመርያው በሕገ መንግሥቱ ሰነድ ላይ የሚነሱ ክርክሮች ሲያጋጥሙ ሲሆን፣ ይኼም ማለት አንድ ሰው የመናገርና የሃይማኖት ነፃነት እንዳለው ተደንግጎ ቢገኝም፣ ሁለቱ ሊጋጩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ በመሆኑም ክፍተቱን ለመሙላት ትርጉም እንደሚያስፈልገው ገልጸዋል፡፡ ሁለተኛው የፍርድ ቤቶች ውሳኔዎች ከሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎች ጋር የሚጋጩ ሆነው ሲገኙ ፈራሽ በማድረግ፣ የሕገ መንግሥት የበላይነትን ማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ሦስተኛው የባለሥልጣናት ውሳኔ ሕገ መንግሥታዊ መብቶችን ሲጥስ ፈራሽ መሆን እንዳበት በመግለጽ፣ ይኼም የሚፈጸመው የሕገ መንግሥቱን የበላይነት ሳይጠብቁ በፓርላማ በሚፀድቁና ለአስፈጻሚ ተቋማት በሚወጡ አዋጆች አማካይነት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የሕገ መንግሥት ትርጉም ለፌዴሬሽን ምክር ቤትና ለሕገ መንግሥት አጣሪ ኮሚሽን መሰጠቱን የገለጹት ጌታቸው (ዶ/ር)፣ ሕገ መንግሥቱ በሥራ ላይ ከዋለ ጀምሮ ከ3,000 በላይ አቤቱታዎች መቅረባቸውን ጠቁመዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 1,600 ያህሉ እስካሁን ውሳኔ አለማግኘታቸውን፣ 1,300 ገና በመታየት ላይ ያሉ መሆናቸውንና 60 አቤቱታዎች ብቻ ለትርጉም ለምክር ቤቱ መቅረባቸውን ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ሲከሰስ ጉዳዩን መርምሮ ውሳኔ ለማስተላለፍ ግዴለሽነት እንደሚታይና ለዚህ ማሳያ ቅንጅት ስብሰባ እንዳያደርግ ሲከላከል፣ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን የከሰሰበትን የክስ ሒደት በምሳሌነት ጠቅሰዋል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የፖለቲካ ተቋም ከመሆኑ አንፃር ተቃራኒ ውሳኔ ይሰጣል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ስለሚሆን፣ ከየክልሎቹ የተውጣጡና ብቃት ያላቸው ዳኞች በሕዝቡ ተመርጠው የሚዳኙበት የሕገ መንግሥት ፍርድ ቤት በማቋቋም ለችግሮች መፍትሔ መስጠት እንዳለበት የሕግ ባለሙያዎቹ አስተያየት አቅርበዋል፡፡ ሕገ መንግሥቱም ተሻሽሎ የትርጉም አሰጣጥ ሥርዓቱም መስተካከል እንዳለበትም አክለዋል፡፡     ", "passage_id": "32fda8fcfc1f3b191df613fc8341038d" }, { "passage": "በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በሚዲያው ዘርፍ የተወሰዱ እርምጃዎች በዘርፉ ለተመዘገበው ለውጥ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን የኢፌዲሪ ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ፡፡ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በኢትዮጵያ መንግስት፣ በአፍሪካ ህብረትና በዩኔስኮ አስተባባሪነት በኢትዮጵያ በመከበር ላይ የሚገኘው 26ኛው አለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት ቀን፥ በትናንትናው ዕለትም በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በተካሄደው ውይይት ቀጥሎ ውሏል። በመርሃ ግብሩ ላይም መገናኛ ብዙሃን በነፃና ፍትሃዊ ምርጫ እንዲሁም በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ላይ ያላቸውን ሚና አስመልክቶ ትኩረት በማድረግ ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኢፌዲሪ ፕሬዚ ዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እንደተናገሩት፤ ባለፈው አንድ ዓመት በተለይም የመናገር ነጻነትን ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በእስር የነበሩ ጋዜጠኞች ተለቀዋል፤ በአንዳንድ ሚዲያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ተነስቷል፤ አፋኝ ህጎችና መመሪያዎችን የማሻሻል ስራ ተሰርቷል፡፡ እነዚህን ተግባራት ተከትሎ የአገሪቱ የሚዲያ ነጻነት ላይ ለውጥ መጥቷል፡፡ ባለፈው አንድ ዓመት ኢትዮጵያ ያከናወነቻ ቸውን በጎ ተግባራት ተከትሎ አገሪቱ በፕሬስ ነጻነት አበረታች ውጤት አስመዝግባለች ያሉት ፕሬዚዳንቷ፤ ይህን ተግባር እውቅና ለመስጠት የዓለም የፕሬስ ነጻነት ቀን በኢትዮጵያ መከበሩ በአገሪቱ የፕሬስ ነጻነቱ ቀጣይነት ያለው ለማድረግ እንደሚረዳ ጠቁመዋል፡፡ እንደ ፕሬዚዳንቷ ማብራሪያ፤ በአገሪቱ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ቢረጋገጥም ትኩረት የሚሹ ተግዳሮቶች ተፈጥረዋል፡፡ በማህበራዊ ሚዲያዎች ምክንያት የአገሪቱ የፖለቲካ ትርክቶች ዋልታ ረገጥ እየሆኑ መጥተዋል፡፡ የሀሰት መረጃና የመረጃ ብክለት ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ አገራትን እየተፈታተነ ነው፡፡ የፖለቲካ ባህሉና ጠንካራ ተቋማት በሌሉባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገራት የሀሰት መረጃዎችን ለመለየትና የመረጃ ብክለትን ለመከላከል የሚያስችል ሁኔታ በሌለበት እውነተኛ ዜናን ከልቦለድ ለመለየት አስቸጋሪ እየሆነ ነው፡፡ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ውይይት አስፈላጊ መሆኑን በመጠቆም፤ የፕሬስ ቀንን በማስመልከት እየተዳረጉ ያሉ ውይይቶችም የራሳቸውን አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ብለዋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ዳይሬክተር ጄኔራል አውድሬይ አዛውለይ፤ ‹‹ኢትዮጵያ 40 ደረጃዎችን በማሻሻል ያስመዘገበችው ውጤት የሚደነቅ ነው።›› ካሉ በኋላ አገሪቷ የፕሬስ ነጻነትን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸውን ተግባራት አጠናክራ መቀጠል አለባት ብለዋል፡፡ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጀርሚ ሃንት እንደተናገሩት፤ ባለፈው አንድ ዓመት ኢትዮጵያ 40 ደረጃዎችን ማሻሻል መቻሏ ትልቅ ስኬት ነው፡፡ የብሪታኒያ መንግስትም በዓለም ዙሪያ የፕሬስ ነፃነትን ለማረጋገጥ ለሚከናወነው ስራ ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል። በዚህ ረገድም በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ኤምባሲ ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ ለ100 ጋዜጠኞች የተለያዩ ስልጠናዎችን መስጠቱን ለአብነት የጠቀሱት ጀርሚ ሃንት ድጋፉን አጠናክሮ ለማስቀጠል በዛሬው እለትም አዲስ የድጋፍ ማእቀፍ ይፋ አድርገዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 25/2011", "passage_id": "076db533120dd7fa5b3f7f693d0f96dd" }, { "passage": "አንዳንድ ጽንፈኛ  ኃይሎች  የአገሪቱ  ህገመንግሥታዊ ሥርዓትን  ለመቀልበስ የሚያደርጉት ጥረት  በህዝቦች  ተሳትፎ   መቀልበሱን  የፈዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ያለው አባተ  ገለጹ ።የ11ኛው የብሔር ፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን አስመልክቶ በሐረር ከተማ የተዘጋጀውን ሲምፖዚየም የከፈቱት የፈዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ያለው አባተ እንደገለጹት  አንዳንድ አክራሪና ጽንፈኛ  ኃይሎች ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመናድ  የሚያደርጉት እንቅስቃሴ በህዝቦች  ተሳትፎ ሊቀለበስ ችሏል ።በአሁኑ ወቅት የአገሪቱ ህገ መንግሥታዊ ሥርዓት  በማይቀለበስበት መሠረት ላይ መገንባቱን   አፈጉባኤው  አያይዘው ገልጸዋል ።የብሔሮች ፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የሚከበረው  ህገ መንግሥቱ በፀደቀበት ህዳር  29  ዕለት መሆኑን የጠቆሙት  አፈ ጉባኤው  በዓሉ  መላው የአገሪቱ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች አገራቸውን  ለመገንባት  የገቡትን ቃል ኪዳን  የሚያድሱበት ነው  ብለዋል ።   የዘንድሮ በዓል  ልዩ የሚያደርገው  መንግሥት በጥልቀት ለመታደስ  ቃል  ገብቶ  ወደ  ተግባር   የተሸጋገረበት  ወቅት ላይ  በመሆኑ ነው ያሉት  አፈጉባኤው  መንግሥትና ህዝብ  በጋራ  ለመታደስ  የሚያደርጉትን ጥረት ለማጣጣል  የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን ህዝቡ መታገሉ  ሥርዓቱ  በጠንከራ  መሠረት ላይ መቆሙን ያመለክታል ብለዋል ።የሐረሪ ፕሬዚዳንት አቶ ሙራድ አብዱላሂ በበኩላቸው የፍቅር ፣ ሰላም፣መቻቻልና የአብሮነት ከተማ ወደ ሆነችው ሐረር  እንግዶችን እንኳን ደህና መጣቹህ በማለት ፤ ህዳር 29 ህዝቦች  መክረውና ዘክረው  የህገ መንግሥቱን መሠረት የተጣሉበት  ዕለት መሆኑን  አስገንዝበዋል  ።ባለፉት ሁለት አሥር ዓመታት ህገ መንግሥቱ የሰብዓዊ፣ ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲሁም   ልማትን ማረጋገጥ  መቻሉን  አስረድተዋል ።የ11ኛው  የብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች  በዓል “ ህገ መንግስታችን፣ ለዴሞክራሲያዊ አንድነታችንና ለህዳሴያችን\"  በሚል መሪ ቃል በታለቀ ድምቀት እየተከበረ ይገኛል ።  ", "passage_id": "3bba6f4d1286d199c0ff3bf5de2ff027" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ተቋማዊ በሆነ መልኩ በአማራ ህዝብ ላይ የሚሰነዘሩ የተሳሳቱ ትርክቶች ጠንካራ የሆነ ማዕከላዊ መንግሥት ለመገንባት እንቅፋት መሆኑ ተገለጸ። የአማራ ክልል ህገመንግሥቱን በትክክል ተግባራዊ በማድረግ ሕብረ ብሔርን ያረጋገጠ መሆኑን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የበይነ መንግሥታት ግንኙነት አስታወቀ። ‹‹የአማራ የአብሮነት እሴቶች ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት›› በሚል መሪ ቃል የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች፣ አርቲስቶችና የተለያዩ የታሪክ ምሁራን በተገኙበት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የበይነ መንግሥታት ግንኙነት የቢሮ ኃላፊ ዶክተር ደስታ ተስፋው እንደገለጹት፤ የአማራ ህዝብ በተሳሳቱ ትርክቶች የተነሳ የሚደርሱበትን በደሎች ተቋቁሞ ለሀገር ሰላም እየሰራ ነው። በብዝሀነት የሚያምን ህዝብ ነው። በአማራ ህዝብ ላይ የሚሰነዘሩ የውሸት ትርክቶች ጥርጣሬን በመፍጠር ህዝቦች በአንድ ሀገር ውስጥ አንድ ሆነው እንዳይቀጥሉና ማዕከላዊ መንግስት እንዳይጠናከር አሉታዊ ሚናን ተጫውቷል። ይህ የውሸት ትርክት የአማራ ህዝብን እንዲሸማቀቅ ከማድረግም በላይ ሀገር እንደ ሀገር ለመቀጠል ስጋት እንዲጋረጥባት አድርጓል።ኃላፊው እንደሚሉት፤ እነዚህ በአማራ ህዝብ ላይ የተቃጡ ትርክቶች ካልቆሙ ሀገር አይረጋጋም። በአሁኑ ወቅትም የእርስ በእርስ ግጭቶች እንዲፈጠሩ በማድረግ ኢትዮጵያ እንዳትረጋጋ አድርጓል። የአማራ ህዝብ አብረውት የሚኖሩ የተለያዩ ብሔር ብሔሮችን እውቅና በመስጠት የራሳቸውን ሀይማኖትና ባህልን እንዲያሳድጉ በማድረግ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።በታሪክ ትምህርት የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪ የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው ‹‹የአማራ የአብሮነት እሴቶችና ተሞክሮዎች›› በሚል ርእስ ባቀረቡት ጥናታዊ ፁሑፋቸው ላይ እንደገለጹት፤ የአማራን የአብሮነት እሴት ከኢትዮጵያ እሴቶች ለይቶ ማየት አይቻልም።አማራ ሰላም ፈላጊና መንፈሳዊ ህዝብ ነው። የራሱ የሆኑ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እሴቶች ባለቤት በመሆኑ ሀይማኖትን ከሀይማኖትና ብሔርን ከብሔር አስማምቶ የሚኖር ህዝብ መሆኑን ገልጸዋል። የአማራ ህዝብ ‹‹ደሃ\nተበደለ ፍትሕ ተጓደለ››\nብሎ ለወገኑ ሰልፍ\nየሚወጣ ነው። ፍትህና\nነጻነት የሚፈልግ፣ ዘርና አካባቢን ሳይለይ ጀግኖችን የሚያወድስና የሚያበረታታ፣ አቃፊና እንግዳ ተቀባይ፣ ሀይማኖተኛ፣ የጥበብ ባለቤት፣ ቀደምትና ለሀገሩ ሲል የሚዋደቅ ጀግና ህዝብ መሆኑን በጥናታቸው ጠቅሰው ነገር ግን በውሸት ትርክት እንዲሸማቀቅ በማድረግ ሀገር እንዳይረጋጋና በስነ ልቦና እንዲጎዳ ሆኗል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የሕግ ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ማናየ ዘገየ ‹‹የተሳሳቱ ትርክቶች፤ መንስኤዎቻቸው ያስከተሉት ጉዳትና መፍትሔዎቻቸው›› በሚል ርእስ ባቀረቡት ጥናት ላይ እንዳስገነዘቡት፤ አማራ ለኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ አበርክቶዎች አሉት። ነገር ግን ካለፉት ሠላሳ ዓመታት ጀምሮ ተቋማዊ በሆነ መልኩ በማንነቱ ብዙ ፈተናዎችን እያስተናገደ ይገኛል። ይህም የሀገር አንድነትን ፈተና ውስጥ ከቶታል፤ ማዕከላዊ መንግሥት የተረጋጋ እንዳይሆን አድርጎታል። ፖለቲከኞች ፖለቲካዊ ፍጆታ ለማግኘት ሲባል ስርዓትንና ህዝብን አንድ አድርጎ በማቅረብ የአማራ ህዝብን ጨቋኝ በማስመሰል ለዘመናት አብረውት በኖሩ ህዝቦች በጥርጣሬ እንዲታይ መደረጉን ጠቅሰው በዚህም የተነሳ የቆዩ የአብሮነት እሴቶች ተሸርሽረዋል ብለዋል። ከዛም አልፎ ዜጎች በሀገራቸው በጥርጣሬ እንዲተያዩ ሆኗል። በሀገር ግንባታ ላይ እንቅፋት ፈጥሯል። ለአክራሪ ብሔርተኝነት መነሻ በርን ከፍቷል። መሰረታዊ የቡድንና የግለሰቦች መብቶች ተናግተዋል። የዜጎች የመዘዋወር መብቶች ተደፍረዋል ሲሉ ገልጸዋል። ዶክተር ማናየ በጥናታቸው ላይ እንደጠቀሱት አሁን እያታዩ ያሉ ግጭቶችን ለማስቆምና ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት ለመፍጠር መንግሥት የውሸት ትርክቶችን በህግ ማስቆም፣ በሀገሪቱ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን የተላበሰ ማህበረሰብን መገንባት፣ አክራሪ ብሔርተኝነትን ወደ ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት መቀየርና በታሪክ ለዘመናት ተጋምዶ የኖረ ማህበረሰብን ለአንድ ሀገር እድገት እንዲቆም ማድረግ ያስፈልጋል።አዲስ ዘመን  የካቲት 15/2012ሞገስ ጸጋዬ ", "passage_id": "46206a53fefc31cf31007288fce71ec3" }, { "passage": "የአማራ ክልል ከዓመት በፊት ከነበሩበት የሠላም ችግሮች በአንጻራዊነት መላቀቁን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ \"አፍራሽና ለውጥ አደናቃፊ\" ያሏቸው ኃይሎች በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች የጥፋት አጀንዳ እና የማንነት ጥያቄዎችን በማንሳት አለመረጋጋት ለመፍጠር መሞከራቸውን ገልጸዋል። ጨምረውም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና በአንዳንድ ስፍራዎች ችግር በመፍጠር ግጭት እንዲከሰትና በሰው ህይወት እንዲሁም በንብረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል ብለዋል። አቶ ተመስገን ይህን የተናገሩት የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በተጀመረበት ጊዜ ሲሆን፣ አቶ ተመስገን የ2012 የአስፈጻሚ አካላት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትንም አቅርበዋል። ርዕሰ መስተዳደሩ በተለይ በክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ላይ እንደተናገሩት አፍራሽ ያሏቸው ኃይሎች \"በማኅበራዊ የትስስር መድረኮች ላይ የሚለቀቁ ሐሰተኛ ትርክቶችን በማሰራጨት ክልሉን ወደ ትርምስ ለማስገባት ሁሉን አቀፍ መንገዶችን ሲጠቀሙ ቆይተዋል\" ብለዋል። ይህንንም ሲያብራሩ የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ ከሚንቀሳቀሱት መካከል በተለይ \"የቅማንት ኮሚቴ ነኝ በሚል ጥላቻን ካነገቡ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ፣ ትራንስፖርት እንዲቋረጥና በከተሞች ነውጥ እንዲሰፍን ያደረጉት ጥረት በቁጥጥር ስር የማዋል ሥራ ተሠርቷል\" ሲሉ ጠቅሰዋል።በክልሉ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሰላም ለማስፈን እርቀ ሰላም እንዲፈጠር መደረጉን የገለጹት አቶ ተመስገን ችግር ሲፈጥሩ የነበሩ ያሏቸው 387 ሰዎች በምህረት እንዲገቡ ተደርጎ አንጻራዊ ሠላምና መረጋጋት ለመፍጠር ተችሏል ብለዋል። \"የፋኖን ስም በመጠቀም በሁሉም አካባቢዎች በሚባል ደረጃ የክልሉን ሕዝብ ላይ ችግር በመፍጠር መንግሥት ሕግን ማስከበር የማይችል ለማስመሰል\" መሞከሩን አስታውሰው ይህንን ችግር በዘላቂነት በሠላም ለመፍታት ጥረት መደረጉን ገልጸዋል። ከዚህም ጋር በተያያዘ ሕግና ሥርዓት ለማስከበር በተደረገው ጥረት 215 በምህረት ሲገቡ 405 ሠላማዊ በሆነ መንገድ እጅ ሰጥተዋል። ፈቀደኛ ያልነበሩ 686 ሰዎች ደግሞ በኃይል እጅ እንዲሰጡ መደረጉን አመልክተዋል። ርዕሰ መስተዳደሩ ለክልሉ ምክር ቤት እንደተናገሩት \"ከመንግሥት መዋቅር ውጪ ሆኖ የተለያዩ አካባቢዎችን ሲያተማርምስ የነበረውን ሕገ ወጥ ኃይል የማፍረስ ሥራም ወርቃማ ነው\" ሲሉ ስኬታማነቱን ገልጸውታል። አክለውም የክልሉ ተወላጆችን መፈናቀል፣ የሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት በተደራጁ ቡድኖችና ግለሰቦች ሲፈጸም የቆየ መሆኑን ጠቅሰው፤ \"ከበስተጀርባው የጸረ ለውጥ ኃይሉ እጅ ያለበትና ሁሉንም ክልሎች የቀውስ ቀጠና ለማድረግ የታሰበ ነው\" ሲሉ ተናግረዋል። \"ለውጥ አደናቃፊው ቡድን\" ያሉት ኃይል የክልሉን ሰላም ከማይፈልጉ ኃይሎች ጋር በመሆን አካባቢውን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ብለዋል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ።ይህ ኃይል \"አሁንም ሕዝብን ለማደናገር ሐሰተኛ መረጃ ሆን ብሎ እየለቀቀ ለዘመናት በአብሮነት የኖረውን የቅማንትና የአማራ ሕዝብ ወደ ግጭት እንዲያመራ እየሠራ ነው\" ሲሉ ከስሰዋል። ርዕሰ መስተዳደሩ በተጨማሪ እንደተናገሩት ለዘመናት በክፉም ሆነ በደግ አብረው የኖሩ በሥጋም ሆነ በደም የተጋመዱ \"የአማራና የትግራይ ሕዝቦችን ለማጋጨት በአማራ አዋሳኝ የትግራይ ክልል አካባቢዎች የተለያዩ ጠብ አጫሪና የትንኮሳ ተግባራት\" እየተከናወኑ እንደሆነ ገልጸዋል። ይህንን \"ትኮሳውና ጠብ አጫሪነት ፈር ለማስያዝ የሚመለከታቸው አካላት እንዲገነዘቡና የክልሉ የትኛውንም ራስን የመከላከል ተግባር ሕዝቡ እንዲደግፍ\" ጠይቀው ይህን መፈጸም ተቀዳሚ ተግባር እንደሆነ ለምክር ቤቱ አሳውቀዋል። ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤው የ2012 ዓ.ም በጀት ሪፖርት ግምገማ፣ የሕግ የበላይነትና በሰላም ማስከበር፣ ኮቪድ-19ን በዘላቂነት መከላከል እና በሌሎችም ክልላዊና አገራዊ ጉዳዮች እንደሚመክር ይጠበቃል።", "passage_id": "807d6f92de04ef049029a29c1b601e59" } ]
19fecc44d8c51ef0ddd21013b4e99ccf
880a9eb18efac4ceb4de8b9c38372c82
ከጭጋጉ ማግስት ነዋሪዎቹን የተቀበለው ገደብ ወረዳ
ክፍለዮሐንስ አንበርብርወይዘሮ ሽታዬ ወትዬ፣ ጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ ጎቲቲ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ምንም እንኳን በአሁኑ ወቅት በመንግስት እና ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት በተሰኘው ግብረሰናይ ድርጅት ድጋፍና አያሌ ጥረት የሠላም አየር መተንፈስ ቢችሉም፤ በ2010 ዓ.ም የጉጂ ኦሮሞዎች እና ጌድኦዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት በሕይወታቸው የማይረሳ ክፉ ጠባሳ ጥሎባቸው ያለፈ ወቅት መሆኑን ያስታውሳሉ።ወይዘሮ ሽታዬ፣ ‹‹በወቅቱ መንታ ወልጄ ነበር። ምንጩ ምንድነው የሚለውን እስከዛሬ በቅጡ በማናውቀው ግጭት አካባቢው የጦር አውድማ ሆነ። ግራ እና ቀኝ እሳት ነው፤ የማያቋርጥ ጥይት ሩምታ ነበር። አዝመራው ወደመ፣ እንስሳት ተዘረፉ። የተገኘውን ቤት ንብረት ማውደምና ማቃጠል ሆነ። ነገሩ የውጭ ወራሪ ጠላት የመጣ እንጂ ወንድማማች በሆኑ ሕዝቦች መካከል የተከሰተ ጊዜያዊ ግጭት አይመስልም ነበር። ከሰፈር ውስጥ ወንድና ሴቱ ሁሉ እግሬ አውጪኝ ብሎ ወደ ጫካ ተሰደደ። እኔም ሁለት ልጆቼን ታቅፌ በእግሩ ድክ ድክ የሚለውን ሌላኛውን ልጄን አስከትዬ ነብሴን ለማትረፍ ወደ ጫካ ብን ብዬ ሄድኩ። መሳሪያ በየአቅጣጫው ያለማቋረጥ ይተኮስ ነበር። በዚህ ጊዜ በእግሩ ይራመድ የነበረው ሕፃን ልጄ ወደየትኛው ሥፍራ እንደተሰወረ ማወቅ አልቻልኩም፤›› ይላሉ በወቅቱ ያሳለፉትን ከባድ ፈተና ሲያስታውሱ።በ2010 ዓ.ም በተፈጠረው ግጭት የመከራው ሰለባ ከሆኑት መካከል በአሁኑ ወቅት የ12ተኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አቡሽ በቀለ ሌላኛው ባለታሪክ ነው። በወቅቱ የተከሰተው ችግር ሲያስታውስ እንባውን መቆጣጠር አልተቻለውም። “እንኳንስ ሰው ሣር ምድሩ ተጨንቆ ነበር። የዓለም ገበያን ትኩረት ይስብ የነበረው የቡና ምድር፤ የደም ምድር ሆኖ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች መሳለቂያ መሆናችን ያሳዝናል። ያኔ! አካባቢው ተወረረ። ቤት፣ ሳር ቅጠሉ ነደደ። የተገኘውን ሁሉ መግደልና መዝረፍ ሆነ። አቅመ ዳካማ ሴቶችና አባቶች ሳይቀሩ ፍዳቸውን አዩ። ሮጦ ማምለጥ ያልቻለ ሰው የጥይት ራት ሆነ። ይህ የሆነው ደግሞ በደስታም በመከራም ተለያይቶ በማያውቅ የአንድ አካባቢ ማህበረሰብ ሲሆን፤ የሆነው ሁኔታ ግን ያሳዝናል፤” ሲል በትካዜ የሆነውን ይናገራል።‹‹ግጭቱ ቢያልፍም የዘመናት ህልማችንን ይዞት ሄዷል። ከ30 ዓመት በፊት አባታችን የሰራው ቤትና በቤቱ ውስጥ የነበረው ንብረት በሙሉ ወድሟል። ያፈራው ጥሪት ወደ ዶጋ አመድ ተቀይሯል። ለነገ ብለን ያሰብነው ለዛሬውም ትውልድ ሳይሆን መጥፎ ታሪክ ልናወራ ተገደናል። አሁን ያለነው በፈጠሪ መልካም ምህረትና ግብረ ሰናይ ድርጅት እገዛ ነው›› የሚለው ተማሪ አቡሽ፤ በአሁኑ ወቅት ግን ትምህርቱን ቢቀጥልም አንድ ዓመት በችግሩ ምክንያት በሠላምና ስንቅ እጦት ትምህርት ማቋረጡን ተናግሯል።የገደብ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሲሣይ ታደሰ በበኩላቸው እንደሚሉት፤ ወቅቱን ለማስታወስና የሆነውን ለመናገር “የጨከነ ልብ” ያስፈልጋል። ያ ችግር እንዳይፈጠር ግን ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይቶች ሲደረጉ ነበር። በአካባቢ ችግሮች ቢኖሩ እንኳን በአባገዳዎችና የሃይማኖት አባቶች ተግሳፅ አፈንግጦ ለንብረት ውድመትና ለሕይወት መጥፋት የሚዳርግ ክስተት አልነበረም። በ2010 ዓ.ም የተፈጠረው ግን በአካባቢ ነዋሪዎች ዘንድ በእጅጉ የከፋ ጠባሳ ጥሎ ያለፈ ነበር።ሆኖም ችግሩ ከተከሰተ ጀምሮ አጎራባች ወረዳዎች፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግስት፣ ኦሮሚያ ክልል መንግስት፣ የፌደራል መንግስትና የሚመለከታቸው አካላት ርብርብ በማድረግ ነገሮች ወደ መደበኛ ሁኔታዎች እንዲመለሱ ጥረት ተደርጓል። በአሁኑ ወቅትም ነዋሪው በመንግስትና ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ትብብር ወደ ቀድሞ ቀያቸው ተመልሰው ኑሯቸውን በተለመደው ሁኔታ እያስኬዱ ለዘላቂ ሠላም ውይይት እየተደረገ ነው። በወረዳው 45ሺ ተፈናቃዮች እና በ13 ቀበሌዎች የሚገኙ 4ሺ200 ቤቶች ተቃጥለው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሲሳይ፤ በተደረገው ድጋፍ የወረዳው ነዋሪዎች ወደ ሰላማዊ መንገድ ከመመለሳቸውም በተጨማሪ፣ በአደጋው 855 ቤቶችና ቤተ እምነቶች በዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት ግብረ ሰናይ ደርጅት ድጋፍ ተመልሶ መገንባታቸውን ተናግረዋል። በችግሩ ለተጎዱ ቤተሰቦችም የምግብና አልባሳት ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ፣ ዶሮዎችና በጎች መሰጠታቸውንም ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት በአርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ አስተባባሪነት በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2013 ሳዑዲ አረቢያ 163ሺ ኢትዮጵያውያንን አገሬ ለቃችሁ ውጡልኝ ብላ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ስታደርስና ኢትዮጵያውያን ሲንገላቱ የተመለከቱ ኢትዮጵያውያን ተቆርቋሪነት የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ደርጅት ሲሆን፤ በኢትዮጵያ አራቱም አቅጣጫዎች ችግሮች ሲከሰቱ በርካታ እገዛዎችን ሲያደርግ መቆየቱን የሚናገሩት ደግሞ ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት የቦርድ አባል ፕሮፌሰር አቻለምየለህ ደበላ ናቸው።ፕሮፌሰር አቻምየለህ እንደሚሉት፤ ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት ከምስረታው ጀምሮ በውጭ እና በአገር ውስጥ ያሉ ኢትዮጰያውያን እክል በገጠማቸው ጊዜ ከአጠገባቸው አልተለየም። ለአብነትም ከቡራዩ፣ ሻሸመኔ፣ ወልቃይትና ጉራፈርዳ በግጭት ሳቢያ ለተፈናቀሉ ዜጎች በሚሊዮኖች የሚቆጠር ድጋፍ አድርጓል። የኮረና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ብሎም ከዓመታት በፊት የቆሼ የቆሻሻ ክምር ተንዶ በዜጎች ላይ ላደረሰው ጉዳትም ድጋፍ አድርጓል።በጌዴኦ በተፈጠረው ግጭት ለተፈናቀሉ ዜጎች በወርልድ ቪዥን አማካኝነት የምግብና የአልባሳት ቁሳቁስ ሲያደርግ ቆይቷል። ከዚህ በተጨማሪም 37 ሚሊዮን 700ሺ ብር በማውጣት በእሳት የወደሙ ቤቶችንን የመገንባትና ነዋሪዎችን ወደቀያቸው የመመለስ ሥራ ማከናወኑንና በቀጣይም ለኢትዮጵያውያን ክብርና ሥም የሚመጥን በጎ ተግባር እንደሚያከናውን እና በመላው ዓለም ድጋፍ የማሰባሰብና አገር የመታደግ ሥራውን እንደሚያጠናክሩ ፕሮፌሰር አቻምየለህ አረጋግጠዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37992
[ { "passage": "  \"ከቦታችን ተነቅለን ስንመጣ የተገባልን ቃል አልተፈፀመም   በሰሜን ጐንደር ዞን የአበርጊና ቀበሌ የግጪ ጐጥ ነዋሪ የነበሩት አርሶ አደሮች፣ በረሃብ ማለቃችን ነው በማለት መንግስት ይድረስልን ሲሉ ጥሪ አቀረቡ፡፡ አርሶ አደሮቹ ግጪ በሚባለው ቦታ ከልጅነት እስከ እውቀት ትርፍ በማምረትና ለማዕከላዊ ገበያ ምርት በማምረት ጥሩ ኑሮ ሲመሩ የነበረ ቢሆንም፣ ቦታቸው በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ በመሆኑ ለፓርኩ ደህንነት ሲባል በ2008 ዓ.ም ከቀዬአቸው ተነስተው ደባርቅ ከተማ መስፈራቸውን ይናገራሉ፡፡ይሁን እንጂ ከቀያችን ስንነሳ የተገባልን ቃል አልተፈፀመም፤ የካሳ ክፍያውም በተገባልን ቃል መሰረት አልተከናወነም፣ ለእኛም ሆነ ለወጣት ልጆቻችን ፕሮጀክት ተቀርፆ ስልጠና ተሰጥቶ የስራ እድል ይፈጠራል የተባለው እውን ባለመደረጉ ያለ ስራ ተቀምጠን በረሃብና እርዛት ተጐድተናል ሲሉ ለአዲስ አድማስ ቅሬታቸውን ገልጠዋል፡፡ የካሳ ክፍያውም ቢሆን ከፍተኛው 2ሚ ብር፣ ዝቅተኛው ደግሞ 1 ሚ ብር እንደሆነ ቢነገረንም፣ የተገባው ቃል አልተፈጸመም፤ በዚህም የተነሳ በተሰጠን መሬት ላይ ጐጆ ቀልሰን የተረፈንን ቀለብ ገዝተን ጨርሰን፣ ላለፉት አራት አመታት ያለ ስራ በመቀመጣችን ለረሃብ ተዳርገናል ሲሉ አማርረዋል፡፡  የ70 ዓመት የእድሜ ባለፀጋው ኡስማን አደም እንደሚናሩት፤ ራሳቸውን ጨምሮ 10 ቤተሰብ ይዘው በደባርቅ ከተማ ያለ ስራ መቀመጣቸው ለችግር እንደዳረጋቸው ይናገራሌ፡፡ ከቀያችን ስንለቅ ትከርማላችሁ ተረጋጉ ካሉን በኋላ ድንገት ተነሱ ብለው ረመዳን ጦም ላይ እያለን ነው የተነሳነው፤ በዚህም የተነሳ ከብቶቻችን፣ እህላችን በጐተራ እንደሞላ በጐቻችን ሁሉ የትም ወድቀው ቀሩ::\" ይላሉ-በቁጭት፡፡ ያም ሆኖ መንግስት የገባልንን ቃል ባለማክበሩ፣ ነዋሪው የ5 እና 10 ሺህ ብር ካሳ ብቻ ተሰጥቶን በከተማው ላይ ፈስሰን፤አሁን በረሃብ እየተሰቃየን እንገኛለን ብለዋል አዛውንቱ፡፡ የግጭ ማህበረሰብ ወጣቶችን በመወከል አቤቱታውን የነገረን ወጣት አደም ሙላት በበኩሉ፤ በከተማው በርካታ የስራ እድሎችና አደረጃጀቶች ቢኖሩም፣ የግጭ ማህበረሰብ ወጣቶችን ዞር ብሎ የሚያየን በማጣታችንና ለከፍተኛ ችግር በመጋለጣችን፣ ሃይማኖታችን ወደማይፈቅደው ሥርቆት እንድንገባ እየተገፋፋን ነው ሲሉ የችግሩን አሳሳቢነት ጠቁሟል፡፡  በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አበባው አዛናው እንደሚሉት፤ እነዚህን 252 አባወራዎች አወያይቶና አሳምኖ ደባርቅ እስከ ማስፈር ድረስ የነበረው ሂደት ትክክል ነበር:: የቦታና የሀብት ግመታውም በፌደራል ካሳ ግመታና አከፋፈል መመሪያ መስት የተከናወነ እንደነበረም ተናግረዋል፡፡ እንደ ሃላፊው ገለፃ፤ ሁሉም አርሶ አደሮች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁጥር ከፍተው የተገመተላቸው ካሳ መግባቱንና የቤት መስሪያ ለእያንዳንዳቸው 250 ካ.ሜ የከተማ ቦታ ማግኘታቸውን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ ይላሉ አቶ አበባው፣ ይሁን እንጂ እነዚህ ሰዎች የተሰጣቸው ብርና ቦታ ብቻ ነው፤ በዚያ ላይ ለከተማ ኑሮ አዲስ በመሆናቸው የአነስተኛና ጥቃቅን ስልጠና ለመስጠት፣ የብድር፣ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ አቅርቦት አመቻችቶ ወደተለያየ ሥራ ለማስገባት ፕሮጀክት ተቀርፆ እቅድ መያዙንም ያወሳሉ:: ይህ በሂደት ላይ እያለ በ2008 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ በተነሳ ቀውስና አለመረጋጋት ሳቢያ  ሁሉም አገርን ወደማረጋጋት በመግባቱ አርሶ አደሮቹ መዘንጋታቸውን ይገልጻሉ፡፡ አርሶ አደሮቹ በተሰጣቸው ቦታ ቤት ሰርተው የተረፋቸውን ገንዘብ ቀለብ እየገዙ በመብላት በመጨረሳቸውና ያለ ስራ በመቀመጣቸው ችግራቸው መጠነ ሰፊ፣ ቅሬታቸውም ትክክል ነው፤ ሲሉ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል:: ስለዚህም መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርግላቸው ይገባል ብለዋል፤ ሃላፊው፡፡  ", "passage_id": "77534a023b18b0ba087b316d7200e46d" }, { "passage": "'ሕንጣሎ ወጀራት' ተብሎ ይጠራ የነበረው ወረዳ ለሁለት ተከፍሎ፤ ወጀራት ራሱን የቻለ ወረዳ ሲሆን፤ 11 ጣቢያዎች ያሉት ሕንጣሎ ደግሞ ሒዋነ ከምትባል ሌላ ወረዳ ጋር እንዲካተት ተደርጓል።\n\nሒዋነ ከምትባለው ወረዳ ጋር እንዲቀላቀሉ የተደረጉት የሕንጣሎ ነዋሪች፤ እራሳችንን የቻለ ሕንጣሎ የተባለ ወረዳ ሊኖረን ይገባል እንጂ ከሒዋነ ወረዳ ጋር መቀላቀል የለብንም የሚል ቅሬታ ነው የሚያነሱት። \n\n• ኢትዮጵያ እና ግብፅ 'ቅድመ ስምምነት' ላይ ደረሱ\n\n• ሩስያ መንግሥቴን በትኛለሁ ስትል ምን ማለቷ ነው?\n\nከነዋሪዎቹ እንደሰማነው አሁን በተጀመረው አዲስ የአስተዳደር መዋቅር፤ ወጀራት ከ1-9 ጣቢያዎች ያሉት ሲሆን ሕንጣሎ ግን ሒዋነ ወደሚባል ወረዳ እንዲቀላቀል ተደርጓል። \n\nታዲያ ነዋሪዎቹ የራሳችን ወረዳ ይኑረን፤ በቅርብ አገልግሎት እንድናገኝ ይሁን በማለት ነው እየጠየቁ ያሉት።\n\n\"ምላሽ ካልተሰጠን ተቃውሟችን ይቀጥላል፤ ወደ ቤታችን አንመለስም\" ይላሉ ነዋሪዎቹ።\n\nቢቢሲ ያነጋገራቸው ነዋሪ \"የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ደብረጽዮን ባመጣው አዲስ አሠራር ፤ ነዋሪዎች ከ10 ኪሎሜትር በላይ ርቀው መገልገል የለባቸውም ሲሉ ነበር። እኛ ግን አሁን ተባረን አገልግሎት ለማግኘት የምንጓዘው ትንሹ ርቀት 30 ኪሎ ሜትር ነው\" ይላሉ።\n\nመንገድ መዝጋት መፍትሄ ነው ወይ? በማለት የተጠየቁት ነዋሪው፤ መንገድ መዝጋት ፍትሃዊ ባይሆንም ፍትህ ስላጣን ነው መንገድ የዘጋነው ብለዋል።\n\n\"ከእኛ መካከልም መቀሌ መሄድ ያለባት አራስ አለች፤ ሕመምተኛ አለ፤ ነገር ግን መሠረታዊ ሕይወታችን አደጋ ላይ ስለወደቀ ነው ይህንን ጊዜያዊ ችግራችንን ብንቋቋም ይሻላል ያልነው። ወረዳችንን አሳልፎ ለሌላ መስጠት ተገቢ አይደለም\" ይላሉ።\n\nየአካባቢው ነዋሪዎች ኮሚቴ ወኪል አቶ ደሱ ፀጋየም ይህንን ጥያቄ ማቅረብ ከጀመሩ ስድስት ወራት መቆጠራቸውን ይናገራሉ። \n\nእርሳቸው እንደሚሉት ቅሬታቸውን ለማቅረብ ያልሄዱበት፤ ያልደረሱበት ቦታ የለም። በወረዳ እና በዞን የሚገኙ የፍትሕም ሆነ የፀጥታ አካላትን አዳርሰዋል። ነገር ግን ያገኙት ምላሽ የለም። \n\n\"እኛ መንግሥት በደነገገው ሕግ መሠረት ሁሉንም አሟልተናል። አንደኛ ከ115 ሺህ ሕዝብ በላይ ነን። ሁለተኛ መንግሥት 'ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ ተጉዞ የወረዳ አገልግሎት ማግኘት የለበትም' ነው የሚለው እኛ ግን ከ30 በላይ ኪሎ ሜትር በላይ ሄደን ነው ይህንን አገልግሎት የምናገኘው፤ ስለዚህ የልማት ጥያቄያችን እንዲመለስልን ነው የምንፈልገው\" ሲሉ ጥያቄያቸውን ለቢቢሲ አስረድተዋል።\n\nነገር ግን ይህንን ጥያቄ ማንሳት ከጀመሩ መንፈቅ ቢሞላቸውም፤ የፖለቲካ አስተዳዳሪዎችን መልስ እንዲሰጧቸው ቢጠይቁም ጆሮ የሰጣቸው የለም።\n\nአቶ ደሱ \"በተቃራኒው በዞንና በወረዳ ፖሊስ አማካኝነት ያስፈራሩን ገቡ፤ ለተቃውሞ የወጡ ነዋሪዎችም መንገድ በመዝጋታቸው ወደ ገበያ የሚሄዱ ከብቶች ሳይቀሩ መንገድ ላይ ነው የዋሉት፤ መንገድ ዝግ ነው፤ ይሄው እንዲህ ከሆነ ቀናት ተቆጥረዋል\" ብለዋል። \n\nከአካባቢው ነዋሪዎች እንደሰማነው መንገዱ በመዘጋቱ ከትናንት በስቲያ እስከ 150 የሚደርሱ መኪኖች መንገድ ላይ ሲጉላሉ እንደነበር አስታውሰዋል።\n\nየነዋሪዎቹን ጥያቄ ይዘን ምላሽ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል አማካሪ አቶ ተሾመ፤ የነዋሪዎቹ ጥያቄ እንደተመለሰላቸው ተናግረዋል።\n\nአቶ ተሾመ \"ወረዳቸው ተመልሶላቸዋል፤ የእነርሱ ጥያቄ የወረዳው ዋና ከተማ ደንጎላት ትሁን ወይስ ሒዋነ የሚል ነው\" በማለት ይህንን ጥያቄ የሚመልሰው ደግሞ የወረዳው ምክር ቤት መሆኑን አስረድተዋል።\n\nጥያቄያቸው አልተመለሰልንም የሚሉት ነዋሪዎች፤ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እንዲያነጋግሯቸው... ", "passage_id": "3115cff83071457d61c4551553639032" }, { "passage": " ግንባር ለግንባር ሆኖ የሸማቹን መምጣት የሚጠባበቀው ነጋዴ፣ ሸማቹ፣ ጫኙ፣ አውራጁ፣ የቀን ሰራተኛው፣ ብቻ የሰው ዘር የቀረ እስከማይመስል ድረስ በአንድ ስፍራ የሚገኝበት። ሁካታው፣ ግርግሩ፣ መገፋፋቱ ትርምሱ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ተረፈ ምርት ክምችት ከእነመጥፎ ጠረኑ፣ በመሃል አስፓልት የሚተላለፈው ተሽከርካሪ፣ ሁሉም የራሱን እንጂ የሌላውን የማያይበት። እንዲህ ያለ ትዕይንት ያለዕረፍት ሳምንቱን ሙሉ የሚስተዋልበት አትክልት ተራ ከትናንት በስትያ ጀምሮ ፀጥ ረጭ ብሏል። ነጋዴዎችም ሆኑ ሸማቾች በሥፍራው የሉም። ዙሪያው በደንብ አስከባሪዎችና በፀጥታ ኃይል እየተጠበቀ ነው። ለንግድ የተዘጋጁት አትክልትና ፍራፍሬዎች ግን ‹‹የገዥ ያለህ›› እያሉ ነው። ለአዲስ ንግድ በጊዜያዊነት በተዘጋጀው ጃንሜዳንም ታዝበናል። ገበያው የተሟሟቀ ባይሆንም ግብይቱ ተጀምሯል። አትክልትና ፍራፍሬ ጭኖ የገባው ተሽከርካሪም ጭነቱን እያወረደ ነበር በስፍራው የደረስነው። መደበኛና ኢ- መደበኛ ነጋዴም፣ በሸማቹም የተደበላለቁ ስሜቶችንም ታዝበናል። በአትክልትና ፍርፍሬ ንግድ ላይ የተለያየ ስሜት የተፈጠረው እና ከአንድ ጎልማሳ ዕድሜ በላይ ያስቆጠረው አትክልት ተራ ወደ ጃንሜዳ የተዘዋወረው የኮሮና ቫይረስ በሽታ በመከሰቱ እንደሆነ ይታወቃል። አብዛኛው ነጋዴ ግን ተለክቶ በተሰጠው ቦታ ላይ ግንባታ በማካሄድ ተግባር ላይ ተጠምዷል። በዚህ ጉዳይ ላይ ሸማቹን፣ የንግዱን ማህበረሰብና የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮን አነጋግረናል። በአዲሱ ጃንሜዳ የንግድ ሥፍራ ያገኘናቸው ሸማች አቶ ቢኒያም አየለ ገበያው ወደ መኖሪያቸው በመቅረቡ ጥሩ ስሜት ፈጥሮባቸዋል። ይሁን እንጂ ገና የተደራጀ ባለመሆኑ መረጋጋት አለመኖሩን ታዝበዋል። በሽታውን ለመከላከል ተብሎ የተወሰደው እርምጃ የሚፈለገውን ውጤት እንዲያመጣ ከጅምሩ የመከላከሉ ሥራ ተጠናክሮ መልክ እንዲይዝ መደረግ እንዳለበት ተናግረዋል። አቶ ቢኒያም ለጊዜያዊ ችግር ቦታው መመረጡን ቢደግፉም ቦታው የእምነት ቦታ ማካሄጃ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሚፈጠር ችግር እንዳይኖር በመንግሥት በኩል ጥንቃቄ እንዲደረግ ሃሳብ ሰጥተዋል። ከመኪና ላይ አትክልት በማውረድ በሳጠራ ለንግድ ሲያመቻቹ ያገኘናቸው አቶ አዳነ በርታ ከለመዱት ቦታ መቀየራቸውና በአዲሱ ቦታ ሥራውን እስኪለምዱ ከፈጠረባቸው ስሜት በስተቀር ያጋጠመውን ወረርሽኝ ለመከላከል የተወሰደውን እርምጃ ይደግፋሉ። ገና መጀመሪያ ንግዳቸው በመሆኑ ብዙ ማለት ባይችሉም ከአርባ ምንጭ ተጭኖ የመጣላቸውን አትክልት በሳጠራ እየሞሉ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች ለሚወስዱ ነጋዴዎች እያመቻቹ ነበር ያገኘናቸው። ለንግድ የሚሆነውን አትክልት ሲያመቻቹ የነበረበት ቦታም ጊዜያዊ እንደሆነና ገና ቋሚ የንግድ ቦታ እየጠበቁ እንደሆነ ነው የገለጹልን። በጃንሜዳ በተሰጣቸው ቦታ ላይ ግንባታ ሲያካሂዱ ያገኘናቸውና ከ20 ዓመታት በላይ በሙዝ ንግድ ውስጥ የቆዩት አቶ በቀለ በረካ መንግሥት ካለው ችግር አንጻር የወሰደውን እርምጃ ቢደግፉም ከነጋዴው ህብረተሰብ ጋር ተወያይቶ የጋራ መፍትሄ አልወሰደም፣ ነጋዴውም ቀድሞ እንዲዘጋጅ አላደረገም የሚል ቅሬታ አላቸው። አትክልት ተራ በነበሩበት ወቅት ለበሽታው ቅድመ ጥንቃቄ መወሰድስለሚገባው እርምጃም በጤና ባለሙያዎች ይተላለፉ የነበሩ ምክሮችና በመንግሥትም ይደረግ የነበረው ጥረት ያልተተገበረው ህጋዊ ባልሆኑ ነጋዴዎች እንደሆነና ያንን ማስተካከል ቢቻል ከነበሩበት የንግድ ቦታ ሊነሱ የማይችሉበት ምክንያት ይኖር እንደነበር ያስረዳሉ። እርሳቸው እንዳሉት፣ በአዲሱ የንግድ ቦታ ውሃ፣ መፀዳጃ ቤት፣ መብራት አልተሟላም። የማዘዋወሩ ተግባር በሽታውን ለመከላከል የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች አብረው መመቻቸት እንደነበረባቸው። የተሰጣቸው 18 ካሬ ቦታ ስፋት ለምርት ማከማቻ ቀርቶ ለንግድም በቂ አይደለም። የሚነግዱት ሙዝ ደግሞ ለቀናት ለመብሰል በቂ የሆነ የሙቀት ቦታ የሚፈልግ በመሆኑ በቀድሞ የንግድ ቦታቸው ላይ ሙዙን የማብሰሉ ተግባር እንዲከናወን መንግሥት እንዲያይላቸው ጠይቀዋል። በመንግሥት የተመቻቸው ምርት የማራገፊያ ሰአትም በፀጥታ ኃይል አስከባሪዎች እየተተገበረ እንዳልሆነ፣ በአመራሮች የሚተላለፈው መረጃና በአስፈጻሚው መካከል ያለመናበብ ክፍተት መኖሩንም ያስረዳሉ። የአራዳ አትክልት ተራ የገበያ ማዕከል አክሲዮን ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘላለም እሸቴ በበኩላቸው እንደገለጹት ማህበራቸው በሽታው ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የሚጠበቅበትን ቅድመ ጥንቃቄ ሲያደርግ ቢቆይም ከእርሱ ቁጥጥር ውጭ የሆኑት መከላከል ባለመቻሉ እርምጃው እንደተወሰደ ይናገራሉ። እርምጃው አግባብነት እንዳለውም ያምናሉ። ሆኖም ግን ይላሉ። ንግዱ በተዘዋወረበት ሥፍራ መሰረተ ልማት ማሟላት እንደሚገባ ገልጸዋል። የንግድ እንቅስቃሴው እንዲሳለጥ ተከታታይነት ያለው ክትትል እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል። አዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መስፍን አሰፋ አንዳንዶቹ ቄሬታዎች አግባብነት የሌላቸው መሆኑን ይገልጻሉ። እርሳቸው እንዳሉት ወደ ጃንሜዳ ከመሸጋገሩ በፊት ከነጋዴው ተወካይ ጋር ውይይት ተደርጓል። በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነትም መረጃ በመስጠትና ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች ተሰርተዋል። ለንጽህና መጠበቂያ በአራት መግቢያ በሮች ውሃ በሮቶ ተመቻችቷል። የሰውና የተሸከርካሪ መግቢያና መውጫን በመለየትም ችግሩን ለመከላከል ጥረት ተደርጓል። መጸዳጃም ተጨማሪ ለመገንባት ታስቧል። ቶሎ ተቀብሎ ወደ ሥራ የመግባቱ ነገር ክፍተት ቢኖረውም አሁን መሻሻሎች እየታዩ ነው። ችግሮች እየታዩ እንደሚስተካከሉና ሙዝ ለማብሰያ ቦታ ለሚፈልጉ በቀድሞ ቦታ እንዲጠቀሙ መፈቀዱን አቶ መስፍን ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 1/2012\nለምለም መንግሥቱ", "passage_id": "85ba45e749d6a1eeee6659af68897ad0" }, { "passage": "የመሬት ክስ ይዘው ከሰሜን ወሎ ዞን ዋድላ ወረዳ ሶስት ቀናት ተጉዘው በሰበር ችሎት ለመዳኘት አዲስ አበባ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገኙት አቶ መርሻ ዋስዬ፤ “በ1983 ዓ.ም በአካባቢው ኮሚቴ በድልድል ያገኘሁት ንብረቴ ነው።” ባሉት መሬታቸው ላይ ዘር ከዘሩ በኋላ ትለቅቃለህ የሚል በደል እንደደረሰባቸው ይናገራሉ። “ይህን በደሌን ይዤ ወደ ወልዲያ ፍርድ ቤት ቀርቤ አቤት ብልም ችግሬን ግራ ቀኝ ሳይረዱ ፈረዱብኝ። ቀጥዬ ወደ ደሴ አቀናሁ፤ እዛም ይግባኝ ብል ሰሚ አጣሁ” ይላሉ። ከቤታቸው ከወጡ ሶስት ቀን እንዳለፋቸው የሚናገሩት አቶ መርሻ፤ አዲስ አበባ ለመድረስ ወልዲያ ሁለት ቀን አድረው ብዙ ተቸግረው መድረሳቸውን ንዴት፣ ቁጭትና ብስጭት በተቀላቀለበት ስሜት ይናገራሉ። በቀጣይ ጉዳያቸው ታይቶ ከሚወሰነው ውሳኔ ባሻገር የቀጠሮ ጊዜው በእጅጉ አሳሰቧቸዋል። አሁንም ጉዳዩ ከዋለ ካደረና ቀጠሮ ከበዛባቸው ዘመድ አስቸግረው የሚሰነብቱበት እንዳሳሰባቸው ከጠቀሱ በኋላ፤ ተመለሱና እረዲያ! “ጭርሱኑ ሁሉን አፈራርሶ ደሃ አደር በሆንኩ ይሻለኝ ነበር” በማለት አጉተመተሙ። ክስ መስርተው ተከሳሽን ወደ ፍርድ ቤት ለማቅረብ ከፍተኛ ችግር እንደገጠማቸው የሚናገሩት አቶ መርሻ፤ በተደጋጋሚ ትዕዛዝ ቢወስዱም ተከሳሽ በኮማንደር በግድ ተገድዶ እንጂ በወቅቱ እንደማይቀርብ ይገልፃሉ። የአካባቢው ቀበሌ እና የእርሻ ጎረቤታቸው ጉዳዩን በሚገባ መርምሮ “መሬቱ መርሻ ዋስዬ በድልድል ያገኘው ነው።” ብለው ቢመሰክሩም፤ ተከሳሹ ዘመድ ስላለው በዘመዱ ሊያጠቃቸው እና ከመሬታቸው ሊያፈናቅላቸው መሆኑንም ነው የሚናገሩት፤በ1983\nዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ሲከራከሩ የነበረው ኮሚቴ “መሬቱ የመርሻ ዋስዬ በድልድል ያገኘው ነው፤ አሁን የያዘው ሰው በቀበሌው ነዋሪ አይደለም፤ አይታወቅም የእሱ ቀበሌ ሌላ ነው፤” እያሉ ቢመሰክሩም በወልዲያም ሆነ በደሴ የተቀመጡ ዳኞች ግን አጠፉት ካሉ በኋላ፤ ሰበር ችሎት ጉዳያቸውን በሚገባ መርምሮ እና አጣርቶ ፍትህ ይሰጣቸው ዘንድ እንደሚማፀኑ ይናገራሉ።ሌሎቹ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያገኘናቸው ከ700 በላይ ባለጉዳዮች ሰላማዊ ሰልፍ በሚመስል መልኩ ተሰባስበዋል። የጋራ ጉዳይ እንዳላቸው ለማወቅ አያዳግትም። ንግግራቸው፣ ውይይታቸው እና ማጉተምተማቸው ተመሳሳይ ይዘት ያለው ነው። ሁሉም ሊባል በሚችል መልኩ አይኖቻቸውን ወደ ላይ ሰቅለው ፎቁን ይመለከታሉ። ሁሉም መናገር እና ሀሳባቸውን መተንፈስ ፈልገዋል። ሁሉም ከመንግስት ፍትህ እናገኛለን በሚል ስራቸውን ትተው ፍርድ ቤት መምጣታቸውን ይናገራሉ። ስሜ አይገለፅ ያሉት እናት፤ ከአስር ዓመት በፊት የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ሲመዘገቡ፤ በወቅቱ መቶ በመቶ የከፈለ ቅድሚያ ይሰጠዋል በመባሉ ከልጆቻቸው ጉሮሮ ነጥቀው ቢቆጥቡም ‹‹ እንደተባለው አልሆነም፤ ዕጣ አልወጣልንም ስለዚህ መንግስት ፍትህ ይስጠን ይሄ ትልቅ በደል ነው።›› ይላሉ፡፡ “ጉዳያችን በፍርድ ቤት የተያዘ ቢሆንም ፍትህ ማግኘት አልቻልንም፡፡” የሚሉት ሌላኛዋ ሴት፤ ቅሬታ ቢያቀርቡም በየጊዜው ለወር እና ለአስራ አምስት ቀን እየተቀጠሩ በመጉላላት ብቻ ከአስር ወራት በላይ መቆየታቸውን ይናገራሉ። “የዘገየ ፍትህ እንደቀረ ይቆጠራል” ካሉ በኋላ፤ ይህን ያህል ሰውን ከማመላለስ ይልቅ አፋጣኝ ምላሽ እንደመስጠት ቀጠሮ እየሰጡ ማመላለሱ ተገቢ አይደለም በማለት ይወቅሳሉ።“ዛሬም እዚህ የተሰባሰብነው ለአንድ ወር ቀጠሮ የተሰጠን በመሆኑ ነው፡፡” የሚሉት ወይዘሮዋ፤ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትን ፕሬዚዳንት ለማነጋገር እና ምላሽ እንዲሰጣቸው መገኘታቸውንም ነው የተናገሩት፤ “አሁን ዕድሜዬ ከሀምሳ አመት በላይ ነው። እሬሳዬ ከቤት ይውጣ ብዬ ጌጤንና ያለኝን ንብረት ሽጬ ገንዘቤን ከፍዬ ይኸው እንከራተታለሁ። በገቡት ቃል መሰረት ቤቱን ካልሰጡኝ በዚህ ዕድሜ የት ልውደቅ?” በማለት የሚጠይቁት ሌላዋ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢ እናት፤ ቤቱ ይሰጠን ብለው ፍርድ ቤት እስከመክሰስ ቢደርሱም ፍትህ አለማግኘታቸውን በምሬት ይናገራሉ።ከሳሾች ይሞግታሉ፤ ፍርድ ቤት ቆመው ከባንክ እና ከቤቶች ኤጀንሲ ጋር በየጊዜው እየተከራከሩ ጊዜ፣ ጉልበትና ተጨማሪ ገንዘብ እያወጡ መሆኑን በማመልከት ነገር ግን ምላሽ በፍጥነት አለማግኘታቸውን ያመለክታሉ፡፡ፍርድ ቤቶች ለተገልጋዩ ፈጣን እና ቀልጣፋ ውሳኔ ለመስጠት የሚቸገሩበት በርካታ ምክንያቶች እንዳሉ የሚናገሩት አቶ ሰለሞን እጅጉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር፤ ፍርድ ቤቱ አሁን ላይ እያሻሻለ የመጣባቸው አሰራሮች ቢኖሩም፤ በህግ ባለሙያው ይሁን በባለጉዳይ መረጃና ማስረጃ ምክንያት የውሳኔ ጥራት ማነስ እንዳለ ጠቁመዋል። ከዚህም ባሻገር በየጊዜው የሚመጣው መዝገብ/ጉዳይ ቁጥሩ እና የዳኞች ቁጥር የማይመጣጠን በመሆኑ የቀጠሮ ጊዜውን እንደሚራዘምም ነው የጠቆሙት፤አዲስ ዘመን የካቲት 2/2012ፍሬህይወት አወቀ", "passage_id": "38909748fe04d1d86790489c9dfd52ea" }, { "passage": "በደረሱን ጥቆማዎችና አስተያየቶች መሠረት ዋና ዋና በሚባሉት የከተማዋ ስፍራዎች ተዟዙረን እንደተመለከትነው ከሆነ ያለው ተጨባጭ ሁኔታና ይዞታ ሲበዛ አሳሳቢ፣ ከፍ ሲልም አስደንጋጭ ነው። ራስን በ”ኮሮና አለ/የለም” እስከ መጠራጠር የሚያደርስ ግድ የለሽ፣ ሃላፊነት የጎደለው፣ ማሰብ መተሳሰብን ያራቀ …. የበርካቶች እንቅስቃሴ ከንፈርን በእጅ አሲዞ ከማስደመም በዘለለ ራስ አሲዞ ያስጮሐል። ችግሩ የቱ ጋር ነው? እኔ ጋር ነው ወይስ እነሱ ጋር? ከማስባል አልፎ ከሌላ ፕላኔት የመጣን እንግዳ የሆን እስኪመስለን ድረስ ባይተዋር ያደርገናል – ያለው እንቅስቃሴና ወሰን ዲካ የሌለው የህብረተሰብ ዝንጋኤ።\nእየተነጋገርንበት ያለው ርእሰ-ጉዳይ ለእርስዎ፤ አስፈላጊውን የመከላከልና መቆጠጠር ሥራ ጥንቃቄና የተፈለገውን ፀረ-ኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መመሪያ ውልፍ ሳይሉ ለሚያከናውኑት ሰው፤ ከራስዎትም አልፈው ለሌላው የሚጨነቁ ዜጋ ይህ ትዝብትና ቀጥለን የምናቀርበው የዓይን ምስክሮች ቃል እንግዳ እንደማይሆን፤ ይልቁንም የእርሶዎንም ትዝብት እዚህ እንደገለፅልንዎት አድርገው እንደሚገነዘቡት ጥርጥር ባይኖርም፤ የዝንጋኤያችንን ጥግ ከተባበሩን ሰዎች አንደበት እንካፈል። \nየደረሰንን ጥቆማና አስተያየት መነሻ አድርገን የቃኘናቸው አካባቢዎች መናኸሪያ/መገናኛ፣ ሳሪስ አቦና ሳሪስ፣ ሜክሲኮና ስድስት ኪሎ – መነን ናቸው። መገናኛ እንደደረስን ያጋጠመን ከተለመደው ቀለል ያለ ግርግርና የወዲያ ወዲህ እንቅስቅሴ ሲሆን በቀጥታ ያቀናነው በቀን 30 ሺህ ሰዎችን ወደ ሚያስተናግደው መናኸሪያ ነበር። እንደገባንም ብዙም ትርምስ ባይኖርም ባሉት ዘንድም የተመለከትነው የደረሰንን ጥቆማና አስተያየት ያረጋገጠ ነበር፤ ማንም በሚባል ደረጃ “አድርጉ” የተባለውን እያደረጉ ያልነበሩና ከነአካቴውም ርህራሄ አልባ ገዳይና ጅምላ ጨራሽ ቫይረስ ስለመኖሩ የሰሙ የማይመስሉ ሰዎችን ነው።\nነገሩን በአንድ አጭር ምልከታ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ መወሰን አይቻልምና በቅርበት የሚያውቁ ሰዎችን ማማተር ግድ ሆነ። ሆነናም ከብዙ እምቢተኞች በኋላ ከትንቢት ጋር ተገናኘን።\nወጣት ትንቢት አበበ የመገናኛ ተርሚናል ተራ አስከባሪ ሲሆን ኮሮናቫይረስ በአገራችን መግባቱ በመንግሥት ከመገለፁ ሁለት ቀን በፊት ወደ መከላከሉና ግንዛቤ ማስጨበጡ ሥራ መግባታቸውን ይናገራል።\n“እኛ ከመነገሩ በፊት ሁለት ቀን ቀድመን ህዝቡን ስናሳስብና የንፅህና መጠበቂያ ቁሶችን ስናቀርብ ነበር” የሚለው ትንቢት ከፖሊስና ታክሲ ማህበራት ጋር በመተባበር 16 ቧንቧዎችን በመናኸሪያው ውስጥና ዙሪያው በመዘርጋት ሰዎች እጃቸውን እንዲታጠቡ ስናደርግ ነበር። መንግሥት ካሳወቀ በኋላም በሚነገረው መሰረት ስንሰራ፣ ሰውም በተነገረው መሰረት እንዲያደርግ ስናደርግ ቆይተናል። ርቀት መጠበቅ፣ የፊት ማስክና የእጅ ጓንት እንዲያደርጉ ስናደርግና ተዛቀማጅ ስራዎችን ስናደርግ ቆይተናል” ሲል ይናገራል።\n“አሁንስ?” ላልነውም “ይሄው እንደምታየው ውሃው አለ፤ የሚታጠብ ግን የለም። ርቀት ጠብቆ የመሰለፉ ነገር አይታይም። ሰው የሚነገረውን መስማት ትቷል። በመሆኑም ሁኔታው አስቸጋሪ ነው።” ሲል የመለሰልን ሲሆን በአካባቢው በሚገኝ የኢትፍሩት መሸጫ ሱቅ አካባቢ የተመለከትነውን ከአጠቃላይ ቫይረሱን ከመቆጣጠርና መከላከል ተግባራት ውጭ የሆነ እንቅስቃሴ በተመለከተ ለጠየቅነውም “እሱ እኛን አይመለከትም፤ ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋምን ነው የሚመለከተው። በዛ በኩል ነው እነሱን ማግኘትና እንዲያሰተባብሩ ማድረግ የሚቻለው።” ብሎናል።\nየሥራ ባልደረባው ኤርሚያስ ሙሴም የትንቢትን ሀሳብ በከፍተኛ ደረጃ ያጠናከረ ሲሆን “ሰው ለራሱም፣ ለልጆቹም፣ ለቤተሰቡም፣ ለአጠቃላይ ህዝቡም እያሰበ አይደለም።” በመሆኑም መንግሥት ደጋግሞ ማስተማር አለበት። ህዝቡም ከዚህ አይነቱ መዘናጋት በፍጥነት መውጣት አለበት።” በማለት አስተያየቱን ገልጾልናል።\nእዛው መናኸሪያው ውስጥ በተተከለ የቀይ መስቀል ድንኳን ውስጥ በየካ ክፍለ ከተማ በደም ልገሳ ማስተባበር ሥራ ላይ ያለችውን ወጣት ዘነበች አስራትንም በጉዳዩ ላይ አነጋግረናት የገለፀችልን ነገር ቢኖር ከትንብት የተለየ ሳይሆን የተለያዩ አካባቢዎች ያጋጠሟትን ሁሉ በማጣቀስ እጅግ የከፋ መዘናጋት፣ አጉል ድፍረት፣ ማሾፍ (የፊት ማስክ አድርጉ ሲባሉ ሁሉ ምኔ ላይ ላድርገው? አይኔ ላይ? የሚሉ) በከተማ ውስጥ መኖሩንና ይህም ምናልባት ዋጋ እንዳያስከፍለን በመፍራት ላይ መሆኗን ነው።\nሳሪስ አካባቢ በመሄድ አግኝተን ያነጋገርነው ሌላው አስተያየት ሰጪ በዶሮ ንግድ ሥራ የተሰማራው ወጣት አቤል በለጠ ሲሆን የሰጠው አስተያየት ከላይኛዎቹ የተለየ ባይሆንም ትኩረቱን በመንግሥትና የሚመለከታቸው አካላት አማካኝነት ህዝቡን የማስተማሩ ነገር ዛሬም ነገም መቀጠል ያለበት መሆኑን ጠበቅ አድርጎ መናገሩ ለየት ያደርገዋል። አቤል እንዳለው ከሆነ ይህ ነገር ቶሎ ቶሎ ካልተሰራበት ከባድ ጉዳት በእኛም ሆነ በአገር ላይ ሊደርስ ይችላል።\nበሌሎች የተዘዋወርንባቸው አካባቢዎችም የተለየና በተሰጠው የባለ ሙያ ምክርና አስተያየት ቫይረሱን የመከላከል ሥራ እየተሰራ ነው ማለት የሚቻልበት ደረጃ ላይ ናቸው ማለት የሚያስደፍር አይደለም። ጭራሽ ተቃቅፈው የሚሄዱ ሰዎችን ማየት ሁሉ የተቻለበት አጋጣሚ ከመኖሩና የመዘናጋቱ ከፍታ ከጣሪያ በላይ መሆኑን ከመታዘብ ተጨማሪ ስህተት ሌላ የተመለከትነው አበረታች ነገር የለም።\nይህን ዜና ለማጠናቀር በሚደረግ መዘዋወር ወቅት በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመንግሥትና ባለሙያዎች የተሰጡ መመሪያዎችን ተግባራዊ ባላደረጉ ተንቀሳቃሽ የከተማዋ ነዋሪዎች ላይ ፖሊስ እርምጃዎችን መውሰዱን ለማወቅ የተቻለ ሲሆን፤ በስድስት ኪሎ አካባቢ ፖሊስ ተመሳሳይ ስህተት የፈፀሙ ሰዎችን በመያዝ ወደ ጃን ሜዳ ጊዜያዊ እስር ቤት ሲወስድ መመልከትም ተችሏል።\nባደረግነው የማጣራት ሂደት ለእርምት የተያዙት ሰዎች የፖሊስ እርምጃ የኮሮናቫይረስን ሥርጭት ከመከላከልና ከመቆጣጠር አኳያ ተገቢና መሆን ያለበት መሆኑን የሚቀበሉት ሲሆን አልፎ አልፎ የመደባደብ ሁኔታ መኖሩን ግን እንደማይቀበሉትና ተግባሩም የሰብአዊ መብት ጥሰት መሆኑን ሲናገሩ ተደምጠዋል።\nእኛም እንላለን፤ የማንትስን ጠባሳ ያየ በእሳት አይጫወትም እንዲሉ እዚያ ማዶ ምን እየሆነ፤ እንዴት እየሆነ፣ የት እየደረሰ እንደሆነ እያየን ከዚህ ከልክ ያለፈ መዘናጋት ውስጥ በፍጥነት እንውጣ።አዲስ ዘመን ግንቦት 7/2012ግርማ መንግሥቴ", "passage_id": "4c238c29bebb1afa88540b3fbe6df24b" } ]
f78a65526538650c216966ca4f4d3fa1
a2c556efd098fd7a747f8d67058974ba
“የህወሓት መኖር ለትግራይ ህዝብ ኪሳራ እንጂ ጥቅም አላስገኘለትም” ሲሉ የትግራይ ተወላጅ ዳያስፖራ አባላት ገለጹ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የህወሓት መኖር ለትግራይ ህዝብ ኪሳራ እንጂ ጥቅም አላስገኘለትም ሲሉ በአሜሪካ፤ በካናዳና በአውሮጳ የምንኖር ዳያስፖራ የትግራይ ተወላጆች ገለጹ፡፡ የፌዴራል መንግስት በክልሉ የወሰደውን የሕግ ማስከበር እርምጃ የሚደግፉ መሆኑንም በውጭ አገር የሚኖሩ (ዳያስፖራ) የትግራይ ተወላጆች የፌደራል መንግስት የጀመረውን ሕግን የማስከበር እርምጃን አስመልክቶ ባወጡት የጋራ የአቋም መግለጫ ገልጸዋል፡፡በመግለጫውም፣ እኛ በአሜሪካ፤ በከናዳና በአውሮጳ የምንኖር ዳያስፖራ የትግራይ ተወላጆች በሀገራችን በተለይም የህወሓት ጁንታ በለኮሰው እሳት ሳቢያ መንግስት እየወሰደ ያለው እልህ አስጨራሽ ሕግንና ስርዓትን የማስከበር እርምጃን አስመልክቶ ማሕበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ተሰባስበን በመወያየት በተስማማንባቸው ሃሳቦች መሰረት የለውጡን አጋርነታችንን እንገልጻለን፤” ብለዋል። በመግለጫው አያይዘው እንዳመለከቱትም፤ “የህወሓት መኖር ለትግራይ ሕዝብ ኪሳራ እንጂ ጥቅም አላስገኘለትም። ህወሓት የትግራይ ሕዝብን ደም፤ ጉልበትና ሃብት ለሶስት ቡድናዊ አላማዎች ተጠቅሞበታል። በዚህም አንደኛ፤ የትግራይ ለጋ ወጣቶችን ከደደቢት እስከ አዲስ አበባ ቤተ መንግስት በትረ ስልጣን ለመጨበጥ እንደመረማመጃ አድርጎ ከተጠቀመባቸው በኋላ እንደ ሳልቫጅ ዕቃ ሜዳ ላይ እንዲወድቁ አድርጓል።ሁለተኛም፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ለጋ ወጣቶች በሁለት ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ደም ለማቃባት ሲባል በኤርትራ በሳሕል በረሃዎች የአሞራ ሲሳይ እንዲሆኑ አድርጓል። ሶስተኛ፣ በትግራይ ሕዝብ ስም የሀገራችን አንጡራ ሀብት በጠራራ ፀሐይ ለመዝረፍ ተጠቅመውበታል። ነገር ግን ከግማሽ በላይ የትግራይ ሕዝብ እስካሁን ድረስ ከውጭ የስንዴ እርዳታ ልመና አልወጣም። ወጣቱ ከዓረብ ሀገር ስደትና ውርደት አልዳነም። የሚበላው ይቅርና ሁሉም የትግራይ ከተሞች የሚጠጣ ንፁህ ውሃ እንኳን ማግኘት አልቻለም፤” በማለት አስረድተዋል።በዚህ መግለጫቸው እንዳስታወቁት፤ የትግራይ ሕዝብ የሚበላና የሚጠጣ ብቻ አይደለም ያጣው ሰላምም ጭምር የጠማው ሕዝብ ነው። ህወሓት ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በትግራይ ምድር ከሰባት ጊዜ በላይ ደማዊ ጦርነት ተደርጓል። አብዛኞቹ የጦርነቱ መንስኤ ደግሞ በማሌሊታዊና አብዮታዊ ዴሞክራሲ የደረቀ የህወሓት ጭንቅላት ያመጣው ጣጣ ነው። ከዚህ ሁሉ የተዛባና ጦረኛ ባህሪው የተነሳ የሚፈጠሩ ግጭቶች በአፈሙዝ ካልሆነ በስተቀር በዴሞክራሲ አግባብ በውይይት ለመፍታት ተፈጥሮው አይፈቅድለትም። ህወሓት ከፌዴራል መንግስት ጋር የነበረው ግጭትም በተመሳሳይ ትዕቢት፤ ንቀት፤ ድንቁርናና ጦረኛ አመለካከት የወለደው መሆኑንም ነው የገለጹት።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37983
[ { "passage": "የክልሉ መንግስት ትናንት አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫ የትግራይ ህዝብ ለፍትህ ሲል ከፍተኛ መስዋእትነት መክፈሉን አስታውሶ አሁንም በሚሰሩ ሴራዎችና ችግሮች ሳይንበረከክ በአንድነት ትግሉን እንዲቀጥልበት ያሳስባል። \n\n\"አሁን እየተወሰደ ያለው እርምጃም በማናቸውም ብሔር ላይ የተለየ ጥቃት የሚፈፀምበት እንዳይሆን፣ መስመር እንዲይዝና ህግን የተከተለ እንዲሆን የትግራይ ህዝብ በከፍተኛ ኃላፊነትና ጥንቃቄ እንዲታገለው\" በማለት ጥሪ አድርጓል። ከሌሎች የአገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ጋር በአንድነት እንዲሰራም ይጠይቃል። \n\n\"የትግራይ ህዝብ ማንኛውም ዓይነት ጭቆናና ባርነት እንደማይቀበል ሁሉ ይህ ሌላው ላይም እንዲሆን አይፈልግም፤ ይሁን እንጂ ሊያጠቃን ለሚመጣ ማናቸውም ኃይል እንደማንምበረከክ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ቃልኪዳናችን ነው\" ይላል መግለጫው። \n\n• \"ሃገሬን ሳላስብ የዋልኩበት፤ ያደርኩበት ቀን የለም\" ብርቱካን ሚደቅሳ\n\n• ሕገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር መበራከት ምንን ያመለክታል?\n\n• እምቦጭ የጣና ቂርቆስ መነኮሳትን ከገዳሙ እያስለቀቀ ነው\n\nበሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና የተጠረጠሩ በርከት ያሉት የመከላከያ ብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ሜቴክና የደህንነት አገልግሎት የቀድሞ ኃላፊዎች በቁጥጥር ስር ላይ እየዋሉ እንደሆነ የፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ አስታውቋል። ትናንትም የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው በቁጥጥር ውለዋል።\n\nቀደም ሲል በተካሄዱት የኢህአዴግ መድረኮች ላይ እንዲህ ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና የሙስና ተግባራት ማስተማሪያ ይሆኑ ዘንድ ህግንና ስርዓትን በተከተለ ፤ ብሄርን መሰረት ሳያደርግ እርምጃ እንዲወሰድ መግባባት ላይ መደረሱንም መግለጫው አክሎ ያትታል። \n\nእንዲሁም እርምጃው እርቅንና ይቅርታን መሰረት ተደርጎ የተጀመረውን ጥረት ወደኋላ የሚመልስ እንዳይሆን ፤ የህግ የበላይነትን ሳይሸራረፍ እንዲፈፀም መግለጫው ያሳስባል። \n\nህዝቡንም አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅና ሊመጣ የሚችለውን ማናቸውንም ጥቃት ከመንግስት ጋር በመሆን ለመመከት እንዲዘጋጅ ይጠይቃል። \n\nእየተወሰደ ባለው እርምጃ የማጣራት ሂደቱ በግልፅነትና ከማንኛውም ኃይል ተፅእኖና ጣልቃ ገብነት ውጪ እንዲሆንም የክልሉ መንግስት ይታገላል ብሏል። \n\nበሌላ በኩል የኦሮሚያ ክልል መንግስት የህግ የበላይነት እንዲከበር እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚያደንቅና ለዚህም አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርግ ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።\n\n ", "passage_id": "56a2f9f903c36c1631797e13690ce731" }, { "passage": "ዶክተር አረጋዊ በርሔ\n\nወደ አገር ውስጥ ስለመመለስ ውሳኔያቸው፣ ከህወሐት ጋር ያላቸውን ልዩነትና ቀጣዩ የትግል መስመራቸውን በማስመልከት ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።\n\nወደ ኢትዮጵያ የሚመለሱት ከረዥም ጊዜ በኋላ ነው፤ አሁን ለመመለስ የፈለጋችሁት ለምንድነው? \n\nበመግለጫችን ላይ እንዳስታወቅነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ ለውጥ እየመጣ ነው። እስከዛሬ ከነበረው አገዛዝ ለየት ያለና ተቃዋሚዎችን እንደ ተፎካካሪ የሚያይ፤ መብታቸውን የሚጠብቅ ሆኖ አግኝተነዋል። እንዲሁም አብሮ ሊያሰሩ የሚችሉ ሁኔታዎች በመፈጠራቸው፤ ይህንን አጋጣሚ ተጠቅመን የኛን ራዕይና አላማ ለህዝቡ ለማሳወቅና ካለው ለውጥ ጋርም አብረን እንድንጓዝ አስተዋጽኦ ለማድረግ ወስነን ነው ለመግባት እየተዘጋጀን ያለነው።\n\nከዚህ ቀደም ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ጠይቃችሁ በጎ ምላሽ እንዳላገኛችሁ ይታወቃል። እስኪ ስለሁኔታው ይንገሩን? \n\nአዎ! ብዙ ግዜ ሞክረናል። በተናጥል እንደ ትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር፤ የተለያዩ ህብረቶች አባል እንደመሆናችን በቡድንም በተደጋጋሚ ሙከራዎች አድርገናል። ነገር ግን የነበረው መንግስት አምባገነናዊ የሆነ ባህሪ ስለነበረው፤ እስካሁን የኛን ጥያቄዎች ውድቅ እያደረገ ነው የመጣው። አሁን ግን ውድቅ የሚያደርግ ሳይሆን ወደ ሃገራችን እንድንገባ የሚወተውት፤ እንድንገባ የሚተባበር አዲስ ሃይል ስለተፈጠረ፤ እኛም ለመግባት ወስነናል። የአዲሱ ለውጥ አራማጆች አሁን በስልጣን ላይ ያሉት የእነ ዶክተር ዐብይ አህመድ ቡድን፤ ተቃዋሚዎችን ከውጪ እየሰበሰበ፣ እየጠራ፣ እየተቀበለና እያስተናገደ ነው። ይህ አይነት ጸባይ ባለፈው መንግስት አልነበረም። አመቺ ሁኔታ እንዳልነበር ሁሉም ሰው ያውቀዋል። \n\nየእስረኞች መፈታትና የማዕከላዊ መዘጋት ውሳኔ አንድምታዎች \n\nመንግስት ጥሪ ከማድረግ ባለፈ በሃገሪቷ ፖለቲካዊ ሁኔታ የናንተን አስተዋጽኦ ለመቀበል መንገዶች ተመቻችተዋል ብለው ያምናሉ?\n\nአንደኛ አያያዛቸውን ስናየው ለጋራ ተሳትፎ የሚተባበሩ መስሎ ነው የታየን። ለምን እንደዚህ አልክ ብባል፤ ተቃዋሚ የነበሩ ሃይሎችን ሲቀበሉ አይተናል። እንደውም በትጥቅ ትግል ተሰማርተው የነበሩትን ሳይቀርም እየተቀበሉ ነው። ሁለተኛ፤ አፍነው ይዘዋቸው የነበሩና ታስረው የነበሩ የተለያዩ የፖለቲካ ተቀናቃኞችን ሲፈቱ አይተናል። ለብዙ አመታት ታስረው የነበሩ የሚዲያ ሰዎችም በአንድ ጊዜ ሲፈቱ አይተናል። ስለዚህ፤ እነዚህ ተጨባጭ እርምጃዎች ናቸው። ከንግግር ባለፈ በተቃዋሚ ወይም በተፎካካሪዎች ላይ ምንም መጥፎ አመለካከት እንደሌለ በተጨባጭ ያመለካክታሉ። ስለዚህ ይሄ ሁሉ ለኛ ትልቅ ተስፋ አሳድሮብናል። ይህ ትንሽ ነው ካልን ደግሞ ራሳችን ገብተን ሰፋ እንዲል፤ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እንዲዳረስ የማድረጉ ኃላፊነት የኛ ነው። ነገር ግን ከውጪ ሆነን እንደዚህ ካላገደረጋችሁ አንገባም የምንልበት ምክንያት ወደ ኃላ መሸሽ መስሎ ነው የሚታየኝ። \n\nወደሃገር ውስጥ ከተመለሳችሁ በኋላ በምን መንገድ ነው ተሳትፎ ለማድረግ ያሰባችሁት? በተጨባጭ የያዛችኋቸው ዕቅዶች አሉ? \n\nዕቅዶች አሉን። በሁለት አቅጣጫ ነው የምንታገለው። የመጀመሪያው የትግራይ ህዝብን ወገኑ፤ እህቱ፤ ወንድሙ ከሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋራ አንድነት፣ ሰላም ፍቅር ስለሚፈልግ ይህን እናስተጋባለን። ይህ እንዲሆንም እንታገላለን። እስካሁን ድረስ የመለያየት ፖለቲካ ነበር የሚራመደው። ስለዚህ የትግራይ ህዝብ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተዋደቀ እንደመሆኑ ኢትዮጵያዊነቱን አስረግጦ ከወገኑ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ ወደ እድገት ጎዳና፣ ሰላም፣ ፍቅርና አንድነት እንዲጓዝ ለመስራት ነው እቅዳችን። ሁለተኛው ደግሞ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ የመጣው ለውጥ መልክ ባለው መንገድ እንዲቀጥልና የጋራ ስርአት... ", "passage_id": "e78f74c8eb0f49a26844744b10eb33b1" }, { "passage": "የኢትዮጵያ፣ ኤርትራና አማራ ክልል ሰራዊት እንዲሁም አፍሪካዊ ያልሆነ ኃይል በትግራይ ህዝብ ላይ ጥቃት እየፈፀሙ ናቸው ብለዋል የክልሉ መሪ ዶ/ር ደብረጽዬን ገብረሚካኤል።በዛሬው ዕለት በሰጡት ማብራሪያ በኢትዮጵያና በኤርትራ መንግሥታት ሰራዊት በሚያዙት ከተሞች ንጽሃን ወገኖች ላይ በግፍ ጭፍጨፋ እየተፈጸመ ነው፤ ንብረትም እየተዘረፈ ነው በማለትም ገልጸዋል።የኤርትራ መንግሥት በዚህ ጦረነት ውስጥ የለሁበትም ማለቱ ይታወሳል።\n", "passage_id": "5cebca1b860b7f7995c49873023cf431" }, { "passage": "ማህሌት አብዱልአዲስ\nአበባ፡-\nየህወሓት ጁንታ በአገሪቱ ህዝብ ላይ ያደርስ የነበረውን ጭቆና እና ግፍ በመቃወማቸውና የሃሳብ ልዩነት በማንጸባረቃቸው በጁንታው አባላትና ደጋፊዎች ከፍተኛ ማስፈራሪያና ዛቻ ሲደርስባቸው እንደነበር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛዋ የትግራይ ክልል ተወካይ ገለጹ። ተወካዩዋ\nየተከበሩ ወይዘሮ ያየሽ ተስፋሁነኝ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እንደገለጹት ድርጅቱን ከተቀላቀሉበት ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ\nጁንታው የህወሓት ቡድን በአገሪቱም ሆነ በመላዉ የትግራይ ህዝብ ላይ ያደርስ የነበረው ጭቆና እና ኢ-ሰብዓዊ\nድርጊት ከፍተኛ በመሆኑ ይህንን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሲቃወሙና ሲታገሉ ቆይተዋል። በተለይም\nበምክር ቤቱ በነበራቸው ቆይታ ሚዛኑን ያልጠበቀና እውነትን መሰረት ያላደረጉ ውሳኔዎች ላይ የሚያምኑበትን ሃሳብ በግልጽ በመናገራቸው ምክንያት በድርጅቱ አመራሮች የተመደቡ ግለሰቦች በስልክና በማሕበራዊ ሚዲያ ዛቻና ማስፈራሪያ ያደርሱባቸው እንደነበር ወይዘሮ ያየሽ ተናግረዋል። ‹‹በፌስቡክና\nበተለያዩ ማሕበራዊ ሚዲያዎች አርፈሽ ካልተቀመጥሽ እንዲህና እንዲያ እናደርግሻለን ከማለትም በተጨማሪ ገንዘብ ተሰጥቶሽ ነው፤ የሚሉ ማስፈራሪያዎች፣ ስድብና ዛቻ ይደርስብኝ ነበር›› ያሉት ወይዘሮ ያየሽ፤ አንዳንዳቹም ለእሳቸው በማሰብና በመስጋት ፊትለፊት መጋፈጥ እንደሌለባቸው ይመክሯቸው እንደነበር ጠቁመዋል። በተለይም መስከረም 25 ቀን 2013 ዓ.ም\nየትግራይ ተወካዮች ምክር ቤት እንዳይገቡ በጁንታው የተላለፈውን ጥሪ ባለመቀበላቸው ምክንያት የቅርብ በሚሏቸው አባላት መገለል ያጋጠማቸው መሆኑንና  ይህም ቡድኑ የሃሳብ ልዩነትን የማይቀበልና ፅንፈኛ ድርጅት መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል። ከዚህም ባሻገር ይህ ድርጊታቸው አባላቱ በስነልቦናዊ ጫና ውስጥ ተሸብበው እንዲኖሩ ያደረገ አሸባሪ ቡድን መሆኑንም በግልጽ እንደሚያስረዳ ወይዘሮ ያየሽ ተናግረዋል። እንደርሳቸው ማብራሪያ አገር ሲመራ የነበረው ይህ ህገወጥ ቡድን ህገመንግሥቱንና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን በመተላለፍ ምርጫ ማካሄዱ አልበቃ ብሎ ከመስከረም 25 ጀምሮ መንግሥት የለም በሚል አገር ለማፍረስና ህገመንግሥቱን ለመናድ ያደረገው ሙከራ ምንም እንኳን ባይሳካለትም በታሪክም ሆነ በህግ ተጠያቂ ከመሆን አያግደውም ብለዋል። በተለይም የኮሮና ቫይረስ በዓለም ደረጃ በተስፋፋበት ጊዜ ምርጫ ማካሄዱ ድርጅቱ ከራሱ ጥቅም ውጪ ለህዝቡ የማያስብ መሆኑን አመላካች መሆኑን ወይዘሮ ያየሽ ጠቁመው፤ ‹‹ምርጫው መራዘም እንዳለበት በባለሙዎች ዓይናችን እያየ፣ አሳማኝ ጭብጥ በዝርዝር እየቀረበ መክረንበት የተወሰነ መሆኑ እየታወቀ›› በጁንታው የተላለፈው ምክር ቤት አትግቡ የሚል ትዕዛዝ ፈፅሞ አሳማኝ እንዳልነበረ ያሳያል ብለዋል። በወቅቱም እሳቸው ውሳኔውን በግልጽ ከመቃወም አልፈው ሌሎች አባላትም ውሳኔያቸውን እንዲያስተካክሉ እና ለወከላቸው ህዝብ ታማኝ እንዲሆኑ መምከራቸዉንም አመልክተዋል። “ጁንታው ህወሓትና የትግራይ ህዝብ አንድ ነው ይላል በመሰረቱ ህወሓትና የትግራይ ህዝብ አንድ ከሆነ ምርጫ ለምን ያስፈልጋል? ለምን ሀብትና ጊዜስ ይባክናል?” ሲሉም የተካሄደው ምርጫ ከአሳማኝነቱ ይልቅ ከመስመር የወጣ ተግባርና ለማንም የማያስተምር እንደነበር አንስተዋል። ብዙሃኑ የትግራይ ህዝብ አሁንም በከፍተኛ ድህነት ውስጥ ነው እየኖረ ያለው የሚሉት ወይዘሮ ያየሽ፤ ከጁንታው ጋር ጥገኛ የሆኑ ጥቂት ሰዎች ካልሆኑ በስተቀር የክልሉ ህዝብ አሁንም በርካታ ችግሮችን እየተጋፈጠ እንደሆነ ጠቁመዋል። ለአብነትም በክልሉ አሁንም ከፍተኛ የውሃ እጥረት አለ፤ ተማሪዎች አሁንም በዳስ ነው እየተማሩ ያሉት፤ በክፍተኛ መጠን እየጨመረ የመጣውን አዲስ ትውልድ በአግባቡ ሊቀርፅ የሚችል ተቋም አልተገነባም ሲሉም አስረድተዋል።‹‹ለምርጫ የሚያባክኑት ገንዘብ ለእነዚህ ሥራዎች ቢውል ኖሮ፤ ጠቃሚ እንደነበር የጠቆሙት ወይዘሮ ያየሽ፤ ቡድኑ የራሱን ጥቅምና ፍላጎት ብቻ የሚያስቀድም እንደነበረና የጁንታው አባላትም በገዢነት መደብ ቁጭ ብለው አድራጊና ፈጣሪ ሆነው የሚቀጥሉበትን ዕድል ሲያመቻቹ መቆየታቸውን ጠቁመዋል። አዲስ ዘመን ታህሳስ 8 /2013 ዓ.ም ", "passage_id": "7ab4c704fe9482d0e95141a0dfc3be88" }, { "passage": "በህወሓት  አመት ትግል ወቅት ህይወታቸውን ላጡ ሰዎች፣ ቤተሰቦችና አካላቸውን ላጡ ታጋዮች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባይ ወልዱ አስታወቁ ፡፡42ኛው የህወሓት ምስረታ በዓል የካቲት 11 በመቐለ የሰማእታት ሐወልት ሲከበር  የትግራይ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አባይ ወልዱና በትግሉ ሂደት ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች ቤተሰቦችም ተሳትፈዋል።አቶ አባይ ወልዱ ለተጎጂ ቤተሰቦች እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ እንዳልሆነ ገልጸው ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።አስከፊውን የደርግ ስርዓት ለመደምሰስ በተደረገው ትግል ሂደቱ ህይወታቸውን ያጡ ቤተሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል።የቤተሰቦቹ ተወካዮችም ልጆቻቸው የከፈሉት መስዋእትነት ፍሬ ማፍራቱን ገልጸዋል።በበዓሉ የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻሊ ሀሰን እና የአማራ ክልል  ተወካይ በሰማእታት ሐውልቱ ስር ለመታሰቢያነት የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል።ከሱዳን ከሀ አከባቢዎች የመጡ አስተዳዳሪዎችም በመታሰቢያ በዓሉ ተሳትፈዋል።ህወሓት የተመሰረተበት የካቲት 11 በዓል በተለያዩ አከባቢዎች እየተከበረ ይገኛል- ምንጭ የትግራይ መገናኛ ብዙኋን ኤጄንሲ።", "passage_id": "06fa6a33938b4acadc8a22d65e508ebe" } ]
a613edea6b4d97c1a4e52f58c69e680f
0705c1c3e2345c10d3643df3aee2e7c5
ወደ ዳካር የሚያቀኑት ቦክሰኞች ተለይተዋል
ለቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝጅግት በቦክስ ስፖርት ኢትዮጵያን የሚወክሉ የቡጢ ተወዳዳሪዎችን ለመምረጥ ከወዲሁ ዝግጅት ተጀምሯል፡፡ ከትናንት በስቲያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የዚሁ ዝግጅት አካል የሆነ ውድድርም ተካሂዷል፡፡ ከዚህ ውድድር የሚመረጡ ስፖርተኞችም ከየካቲት 9 እስከ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ በሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር በሚካሄደው የአፍሪካ ቦክስ ቻምፒዮና ላይ በመሳተፍ ወደ ቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚወስዳቸውን ውጤት ለማስመዝገብ የሚፋለሙ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ያዘጋጀው ይህ የብሔራዊ ቡድን ምርጫ የቦክስ ውድድር በአዲስአበባ ስታዲየም በደማቅ ሁኔታ ሲካሄድ በውድድሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ የቦክስ ተወዳዳሪዎች በሁሉም ኪሎ ካታጎሪ የተዘጋጁትን ውድድሮች ማሸነፍ ችለዋል።በውድድሩ ከ52 እስከ 75 ኪሎ ግራም ስድስት ጨዋታዎች የተደረጉ ሲሆን፣ በ52 ኪሎ ግራም የአዲስ አበባ ፖሊሱ ዳዊት በቀለ ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ቦክሰኛው ያዕቆብ በለጠ ጋር ተገናኝተው ዳዊት ማሸነፍ ችሏል፡፡ በ57 ኪሎ ግራም የድሬዳዋ ብቸኛ ተወካይ የሆነው አብዱልሰላም አቡበከር ከአዲስአበባ ፖሊሱ ፍቅረሰላም ያደሳ ጋር ተገናኝተው ብርቱ ፋክክር ቢያደርጉም ፍቅረሰላም ያደሳ አሸናፊ መሆን ችሏል።በ63 ኪሎ ግራም የአዲስ አበባ ፖሊስ ተወዳዳሪ አብርሃም ዓለም የፌዴራል ፖሊሱን ተጋጣሚ ሲያሸንፍ ፤ በተመሳሳይ በ69 ኪሎ ግራም የአዲስ አበባ ፖሊሱ መስፍን ብሩ የፌዴራል ፖሊሱን ቢኒያም ተስፋዬን አሸንፏል። በመጨረሻ በተካሄደው 75 ኪሎ ግራም ውድድር የአዲስ አበባ ፖሊሱ ተመስገን ምትኩ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ተጫዋች ከሆነውን ባምላኩ ደጉ ጋ ተጋጥሞ በዳኛ ውሳኔ ማሸነፍ ችሏል።በሌላ በኩል በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል በተካሄደው የ63 ኪሎ ግራም የወዳጅነት ውድድር ኢትዮጵያዊው ካሳሁን ሀይሉ እና ቢኒያም ተስፋጋብር ተገናኝተው ካሳሁን ሀይሉ በጠባብ ውጤት አሸንፏል።በውድድሩ በርካታ የቦክስ አፍቃሪያን ተገኝተው የተከታተሉት ሲሆን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሸን ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ፣ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን አመራሮችና ሌሎች እንግዶች በውድድሩ ቦታ በመገኘት ጨዋታዎችን ተከታትለዋል፡፡ ለአሸናፊዎችም ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር እና ሌሎች እንግዶች የሜዳልያ ሽልማት አበርክተዋል።የውድድሩ ዋና ዓላማ በሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር ከየካቲት 9/2012 ዓ.ም ጀምሮ የ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ ጨዋታ ለሚካሄደው የአፍሪካ ማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ ስፖርተኞችን ለመምረጥ ነው። በዚህም መሠረት በውድድሩ አሸናፊ የሚሆኑ ቦክሰኞች በቀጥታ ወደ ዳካር እንደሚያቀኑ ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን  ጥር 10/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=25862
[ { "passage": " ቦጋለ አበበ የ20ኛው ቶታል ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጥር 2 ቀን ይካሄዳል። የውድድሩ ምዝገባ ባለፈው ታህሳስ 2 ቀን የጀመረ ሲሆን ፣ተሳታፊዎች በያሉበት የአሞሌን መተግበሪያ በመጠቀም ምዝገባውን እንዲያካሂዱ ተደርጓል ። የመጀመሪያዎቹ 200 ተሳታፊ ተመዝጋቢዎች ለውድድሩ መዘጋጃ የሚሆን የመለማመጃ ቲ-ሸርት በነጻ እንደሚሰጣቸውም የውድድሩ አዘጋጆች ከላኩት መግለጫ ታውቋል። 20ኛው ቶታል ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በዘንድሮ ውድድሩ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ 12ሺ500 ተሳታፊዎች ብቻ ይኖሩታል። በተጨማሪም የአለም አቀፍ ተሳታፊዎችን ለማካተት ውድድሩ በሚካሄድበት ተመሳሳይ ቀን በቨርቹዋል ውድድር በያሉበት ተሳታፊ እንዲሆኑና የ20ኛውን አመት ክብረ በዓል አብረው እንዲያከብሩ ቅድመ ሁኔታ ተጠናቋል። የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ መሰረት ከቀድሞ ተሳታፊ 25 በመቶ ብቻ አሳታፊ የሚያደርገው ታላቁ ሩጫ የሚከተሉትን የኮቪድ-19 ቅድመ ጥንቃቄዎች ተግባራዊ ያደርጋል። ውድድሩ የሚጀመረው በሶስት የተለያዩ ማዕበሎች(አረንጓዴ፤ ቢጫ፤ ቀይ) ይሆናል። ሶስቱ ማዕበሎች ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጡበት አቅጣጫ በየቲሸርት ቀለሙ ተለያይቶ የተሰየመ ነው። እያንዳንዱ ማዕበልም ማህበራዊ ርቀትን ለማስጠበቅ ሲባል በ 3 እና በ4 ቡድን ይከፈላል። ሩጫው በሶስት የተለያዩ መነሻ ሰዓታት የሚደረግ ይሆናል፤ ተሳታፊዎች የሚጀምሩበትን ሰዓት እና አብረው የሚሮጡትን ቡድን ለመለየት ከሩጫ ቲ-ሸርታቸው ጋር አብረው የሚወስዱት የደረት የመሮጫ ፊደል ጠቋሚ ይሆናል። እያንዳንዱ ተሳታፊ ከሚመርጠው የቲ-ሸርት ቀለም ባሻገር የመወዳደሪያ የደረት ቁጥር በፊደል የሚወስዱ ይሆናል። ተሳታፊዎች የመሮጫ ቲ-ሸርታቸውን ሲወስዱ አብሮ የሚሰጣቸውን የአፍና አፍንጫ ጭንብል የውድድሩ መነሻ፤ የመሰበሰቢያ ቦታና ውድድሩን ከጨረሱ በኋላ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ከዚያም በተጨማሪ ተሳታፊዎች መወዳደሪያ ቦታው ላይ እንደደረሱ እያንዳንዱ ተሳታፊ የሰውነት ሙቀት ልኬት ይደረግለታል።እንዲሁም በውድድሩ መነሻና መድረሻ የእጅ ማጽጃ ሳኒታይዘር ይቀርባል። ‹‹ወፎችን ታሳቢ ያደረገ የሀይል መሰረተ ልማት›› የ2013 የሩጫው መልዕክት ሲሆን፣ ‹‹በርድ ላይፍ አፍሪካ- የነጩ ጆፌ አሞራ ፕሮጀክት›› የዚህ መልዕክት አስተላላፊና አጋር ድርጅት ነው።የዚህን ዓመት ታላቁ ሩጫ ለየት የሚያደርገው የውድድሩ መነሻ መስቀል አደባባይ ሆኖ መድረሻው አትላስ አካባቢ መሆኑ ነው። ተሳታፊዎች ውድድሩ ሊካሄድ 10ቀናት ሲቀሩት የመወዳደሪያ ቲ-ሸርት፤ የመሮጫ የደረት ቁጥር ፊደል እና ጭምብል ምዝገባ ሲያደርጉ በመረጡዋቸው የዳሽን ባንክ ቅርንጫፎች በመሄድ መቀበል ይኖርባቸዋል።  አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 5/2013", "passage_id": "1c88714479b8677ce89eed85faa70f55" }, { "passage": "ለአምስተኛ ጊዜ የሚካሄደው ዓመታዊዉ የኮፓ ኮካ ኮላ እግርኳስ ውድድር ይፋዊ የመክፈቻ መርሐ ግብር በዛሬው እለት የኮካ ኮላ ኩባንያ ፣ ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ አ.ማ. እንዲሁም የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ኃላፊዎች በተገኙበት በካፒታል ሆቴልና ስፓ ተካሂዷል፡፡በመግለጫውም የዘንድሮው ውድድር ለሚቀጥሉት ሦስት ወራት በመላው ሀገሪቱ 2,500 የወንድና ሴት ቡድኖችን እንደሚያሳትፍ የተገለፀ ሲሆን እድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ከ45,000 በላይ ታዳጊ ወጣቶች መካከል ውድድሩ ይካሄዳል፡፡ ከዚህ ውስጥ 500 ትምህርት ቤቶች በሪሳይክሊንግ ፕሮግራም ላይ ተሳትፈው ፣ የተለያዩ አሮጌ የፕላስቲክ ጠርሙሶች በመሰብሰብ ለትምህርት ቤታቸው የእግርኳስ ሜዳ የማሸነፍ እድል ያገኛሉም ተብሏል፡፡አቶ ዓለም ዓለማየሁ የኮካ ኮላ ፍራንቻይዝ ስራ አስኪያጅ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ላይ የውድድሩን ጠቀሜታ አውስተው የዘንድሮው ውድድር ከእግርኳስ ውድድሩ ጎን ለጎን በትምህርት ቤት ውስጥ የሚገኙ ታዳጊዎችን በቆሻሻ የተበከለ አካባቢያቸው በሪሳይክሊንግ እንዴት ማፅዳት እንደሚችሉ ለማስተማር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፤ በዚህም የፕላስቲክ ጠርሙሶችንና ቆርኪዎችን ለሰበሰቡ ትምህርት ቤቶች ኮካ ኮላ እውቅና ሰጥቶ እንደሚሸልምም ገልፀዋል። በዚህም አሸናፊ የሚሆነው ትምህርት ቤት የእግርኳስ ሜዳ የሚያሸንፍ ሲሆን ሁለተኛና ሦስተኛ የሚወጡት ትምህርት ቤቶች መጽሐፍት ፤ የትምህርት ቁሳቁሶች እና መሳሪያዎች በቅደም ተከተላቸው እንደሚያሸንፉ ገልፀዋል፡፡በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፀሐፊ የሆኑት አቶ ሰለሞን ገ/ሥላሴ እንደተናገሩት የዚህ አይነት ፕሮግራሞች መካሄድ የሀገራችንን እግርኳስ ከማዳበር በዘለለ ተዳጊዎችን በማነሳሳት ፣ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ ለመርዳትና ወደፊት የተሻለ ተጫዋቾች ሆነው እንዲገኙ የሚያደርጉ ስለመሆናቸው ተናግረዋል፡፡በመቀጠልም ይሰብስቡ ፤ ያሸንፉ በማለት ዘንድሮ ኮካ ኮላ ከውድድሩ ጎን ለጎን ስለሚካሄደው የማኅበራዊ አገልግሎትን በተመለከተ ገለጻ በወ/ሮ ምህረት ተክለማርያም ቀርቧል፡፡በመጨረሻም ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥተዋል። ከተነሱት ጥያቄዎች መካከል ስለውድድሩ የሚካሄድበት ወቅት የተጠቀየቁት አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴ ሲመልሱ ውድድሩ በሶስት እርከኖች ተከፋፍሎ የሚካሄድ ሲሆን በተማሪዎች መካከል የሚደረገው የመጀመሪያ የውድድር እርከን ከሰኔ 15-30፤ ከሐምሌ 10-20 ድረስ ደግሞ በክልል ደረጃ ውድድሩ ሲቀጥል በስተመጨረሻም ከሐምሌ 20-30 ድረስ ሀገር አቀፉ የማጠቃለያ ውድድር የሚካሄድ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡", "passage_id": "99f100333670ca5b6e0081347d734645" }, { "passage": "የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴዎድሮስ አሸናፊ ፋውንዴሽን በ25 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባውን የጎዳና ላይ ልጆች ማቋቋሚያ ማዕከል ተረከበ፡፡ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የተገነባው ማቋቋሚያ ማዕከል ወጪው ሙሉ በሙሉ በፋውንዴሽኑ የተሸፈነ ሲሆን፣ 2‚000 ታዳጊዎችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው ተገልጿል፡፡ማዕከሉ 280 የመኝታ ክፍሎች፣ የመጀመርያ ዕርዳታ መስጫ ክሊኒክ፣ ሁለት የአስተዳደር ቢሮ መገልገያዎች፣ አንድ የመመገቢያና የቴሌቪዥን መመልከቻ ክፍል አለው፡፡ እንዲሁም 36 የቁም ገላ መታጠቢያ፣ ስምንት መፀዳጃ ቤቶችና 16 የልብስ ማጠቢያ ገንዳዎች አሟልቶ ይዟል፡፡የፋውንዴሽኑ ሊቀመንበር አቶ ቴዎድሮስ አሸናፊ ማዕከሉን፣ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ተፈራ አስረክበዋል፡፡ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ የመጣው የጎዳና ተዳዳሪ ልጆች ብዛት አሳሳቢ የማኅበራዊ ችግር እንደሆነ ተነግሯል፡፡ በቅርቡ ለተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የጎዳና ላይ ልጆች ተጋላጭ መሆናቸው ችግሩን የበለጠ አስከፊ እንደሚያደርገው ተጠቁሟል፡፡ይህንን ማኅበራዊ ቀውስ በመመልከት በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተጀመረውን የጎዳና ላይ ልጆች ማቋቋሚያ ፕሮጀክት ለመደገፍ፣ ፋውንዴሽኑ 2‚000 ታዳጊዎችን ሊያስተናግድ የሚችል ማቋቋሚያ ማዕከል ገንብቶ ማስረከቡን አስታውቋል፡፡በርክክቡ ሥነ ሥርዓት ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ጎዳና ላይ የወደቁ ዜጎችን መልሶ በማቋቋም ላይ እንደሆነ አቶ ሙሉጌታ ተናግረዋል፡፡ አስተዳደሩ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከሚደገፉ ስምንት አገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር 2‚000 ዜጎችን ከጎዳና ላይ ማንሳቱን አስረድተዋል፡፡ ኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንድ ዲቨሎፕመንት የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት 1‚200 ዜጎችን ከጎዳና ላይ እንዳነሳም ገልጸዋል፡፡ አስተዳደሩ 300 የሚሆኑ ዜጎችን አቃቂ በሚገኘው መልሶ ማቋቋሚያ እንዳስገነባ ጠቁመው፣ በአጠቃላይ በሁለት ወራት ውስጥ 3‚500 ዜጎችን ከጎዳና ላይ ማንሳት እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ አስተዳደሩ ከመቄዶኒያ፣ ስምንት መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች፣ ኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንድ ዲቨሎፕመንትና በራስ አቅም በድምሩ 11‚000 ዜጎችን ከጎዳና ላይ ለማንሳት እንደታቀደ አስረድተዋል፡፡‹‹ቴዎድሮስ አሸናፊ ፋውንዴሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ላስተላለፉት ጥሪ አፋጣኝ ምላሽ ሰጥቷል፤›› ያሉት አቶ ሙሉጌታ፣ ፋውንዴሽኑን ገንብቶ ያስረከበው ማዕከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጀመረው የጎዳና ላይ ልጆችን የማንሳት ፕሮጀክት ትልቅ ዕገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡ማዕከሉ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን መልሶ ለማቋቋም የተለያዩ ሥልጠናዎች ለመስጠት እንደሚጠቅም ገልጸዋል፡፡ ለወጣቶቹ የሥነ አዕምሮና የሙያ ሥልጠናዎች በመስጠት ወደ መደበኛ ሕይወት እንዲገቡ እንደሚደረግ አስረድተዋል፡፡የፋውንዴሽኑ ሊቀመንበር የመልሶ ማቋቋሚያ ማዕከሉ ግንባታ የተጠናቀቀው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በተስፋፋበት ወቅት በመሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ኅብረተሰቡና መንግሥት ለሚያደርጉት ወረርሽኙን የመቆጣጠር ጥረት ዕገዛ ያደርጋል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ መንግሥት የጀመረውን የጎዳና ላይ ልጆች የማቋቋም ጥረት የንግዱ ማኅበረሰብ፣ የሲቪል ማኅበረሰብና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ዕገዛ አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡", "passage_id": "d011ad249a411dc6240ff90c0a5f3b3b" }, { "passage": "ሦስት ሰዎች የተጎዱበት ከኮርማዎች ጋር የተደረገ ሩጫ\n\nበስፔን በሚካሄደው ከነውጠኛ ኮርማዎች ጋር የመሯሯጥ ዓመታዊው ሳን ፌርሚን ፌስቲቫል ላይ 2 አሜሪካዊያንና የስፔን ዜጋ ላይ ጉዳት መድረሱን ባለስልጣናት አስታወቁ። \n\n• የኢትዮ ቴሌኮም 49 በመቶ ድርሻ ለሽያጭ ይቀርባል ተባለ\n\nበቀይ መስቀል ህክምና የተደረገላቸው በጠቅላላው ቀላል ጉዳት ያስተናገዱ ሰዎች ቁጥር ወደ 48 እንደሚጠጋ ባለስልጣናቱ ጨምረው አስታውቀዋል። \n\nፌስቲቫሉ እስከ የፊታችን እሁድ የሚቀጥል ሲሆን ከኮርማው ጋር መሯሯጡ ጠዋት ጠዋት ላይ ይካሄዳል። \n\nበፌስቲቫሉ ላይ የሚሳተፉት ሰዎች ነጭ ልብስ እና ቀይ ስካረፍ በማድረግ በጠባብ ጎዳና ላይ ለ850 ሜትር ከበሬ ፊት በመሮጥ ለኮርማዎች ወደ ተከለለው ቦታ ድረስ ከኮርማው ጋር ይሯሯጣሉ። \n\n• ጥሩ ሰው ምን አይነት ነው? \n\nበየቀኑ ስድስት ኮርማዎች ይለቀቃሉ በዚህም በርካቶች ጉዳት ይደርስል። ይህ ጥንታዊ ፌስቲቫል ከ1910 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን እስካሁን 16 ሰዎች በኮርማዎች ተወግተው ህይታቸው አልፏል። \n\nለመጨራሻ ጊዜ አንገቱ ላይ ተወግቶ ህይወቱ ያለፈው ዳኒኤል ሮሜሮ 2009 ላይ ነበር።\n\nትናንት ጉዳት ያስተናገደው የ46 ዓመቱ አሜሪካዊም አንገቱ ላይ እንደተወጋና ቀዶ ህክምና እንደተደረገለት አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል።\n\nበዚህ ፌስቲቫሉ ላይ ለመሳተፍ በርካቶች ከመላው የዓለማችን ክፍል ወደ ስፔን ያቀናሉ። ዕድሜው ከ18 ዓመት በላይ የሆነ ሁሉ በፌስቲቫሉ ላይ መሳተፍ የሚችል ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ተሳታፊ ሆነው የሚታዩት ግን ወንዶች ብቻ ናቸው። \n\nከኮርማዎች ፊት የመሯሯጥ ፌስቲቫል በእንስሳት መብት ተሟጋቾች ከፍተኛ ተቃውሞ ይቀርብበታል። \n\n ", "passage_id": "52d6d82b87402556751ccb36baccbf33" }, { "passage": " በቀድሞ ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች የተቋቋመውና በራሊ ፉትቦል ዴቨሎፕመንት ስር የሚገኘው ፓሽን ስፖርት አካዳሚ ከ10 አመት ጀምሮ ያሉ ታዳጊዎችን በመያዝ ማሰልጠን ከጀመረ አመት አልፎታል፡፡ ቡድኑ ከሌሎች የሃገራችን የታዳጊ ቡድኖች በተለየ በውጭ ሃገራት በሚዘጋጁ የታዳጊዎች ውድድር ላይ በመካፈል ለታዳጊዎች ከወዲሁ የኢንተርናሽናል ጨዋታዎች ልምድ እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል፡፡አካዳሚው አምና በቺካጎ በተደረገው ውድድር የተሳተፈ ሲሆን 3 ጨዋታዎችን አድርጎ መመለሱ የሚታወስ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ነገ በሚጀመረውና በሁለቱም ፆታዎች ከ11 አመት እስከ 18 አመት በሚገኙ የእድሜ እርከኖች በመቶዎች የሚቆጠሩ ቡድኖችን ባሰባሰበው የጎቲያ ውድድር ላይ በ14 አመት በታች ቡድኑ ለመሳተፍ ተዘጋጅቷል፡፡ይህ ውድድር ከአዲስ አበባ በ5900 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው በስዊድኗ ጉተንበርግ ከተማ ሲካሄድ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች የሆኑትን ፒኤስጂ ፣ ኒውካስል ዩናይትድ እና አያክስ አምስተርዳምን ጨምሮ 1700 ቡድኖች ፣ ከ50ሺህ በላይ ታዳጊዎች እና አጠቃላይ የልኡካን ቡድን ይሳተፉበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከ100 በሚልቁ ሜዳዎች 4000 ጨዋታዎች የሚካሄድበት እና 500 ዳኞች በሚሳተፉበት ውድድርም በነገው እለት በኡሌቪ ስታድየም የመክፈቻው ስነስርአት ይካሄዳል፡፡ይህ ውድድር በ1970ዎቹ አጋማሽ ከ5 ሃገራት በተውጣጡ 275 ቡድኖች የተጀመረ ሲሆን በ2014 የተሳታፊዎች ቁጥር 73 ሃገራት እና 1670 ቡድኖች ላይ መድረስ ችሏል፡፡ በአእምሮ እድገት ዝግመት ለተጠቁ ታዳጊዎች የተዘጋጀና በቀድሞው የስዊድን ብሄራዊ ቡድን እና ኦሎምፒክ ሊዮን ኮከብ ኪም ካልስትሮም ስፖንሰር የሚደረገው ውድድርም የዚህ ፌስቲቫል አንዱ አካል ነው፡፡በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ የሚያስፈልገው ክፍያ 100 ዩሮ ሲሆን የአካዳሚው ባለቤቶች ከወራት በፊት ከኢትዮጵያን ቢዝነስ ሪቪው ጋር ባደረጉት ቆይታ ለኢንተርናሽናል ውድድሮች ወደ ውጪ ሃገራት ሲጓዙ የትራንስፖርት እና ሌሎች ወጪዎችን የሚሸፍኑት የተጫዋቾቹ ቤተሰቦች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ", "passage_id": "d3c1e6c037bb44e4c84de2fa352dac47" } ]
35d7eb24115e1b4a69cd9067b54611f6
eaa1748dbf96270b2511e420391a2253
የለንደን ማራቶንን የተቀላቀሉ ኮከብ ኢትዮጵያውያን
አትሌት ሞስነት ገረመውና ሙሌ ዋስይሁን በመጪው ሚያዝያ በሚካሄደው የለንደን ማራቶን ከዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ ጋር ከሚፎካከሩ አትሌቶች መካከል እንደሚካተቱ አረጋግጠዋል። ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ባለፈው ዓመት የለንደን ማራቶን ውድድሩን አራት ጊዜ በተከታታይ ካሸነፈውና የቦታውን ክብረወሰን ከጨበጠው ኬንያዊ አትሌት ኪፕቾጌ ተከትለው በመግባት ሁለተኛና ሦስተኛ ሆነው ማጠናቀቃቸው ይታወሳል። ይህም ባለፈው ዓመት ከአንድ እስከ ሦስት በውድድሩ ማጠናቀቅ የቻሉ አትሌቶች ዘንድሮም የሚፎካከሩበት ዕድል እንዲፈጠር አድርጓል። አምና በውድድሩ አራተኛ፣ ካቻምና ደግሞ ሦስተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ የቻለው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ ቀደም ብሎ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን እንደሚወዳደር ያረጋገጠ አትሌት ነው። ሞስነት ገረመው ባለፈው የለንደን ማራቶን ሁለተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡02፡55 የሆነውን የዓለም አምስተኛ ፈጣን ሰዓት ማስመዝገብ የቻለ ሲሆን ክረምት ላይ ተካሂዶ በነበረው የዶሃው የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ማጥለቅ ችሏል። በተመሳሳይ ባለፈው ለንደን ማራቶን ሦስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡03፡16 ሰዓት ያስመዘገበው ሙሌ ዋስይሁን የዓለማችን አስራ አንደኛው ፈጣን ሰዓት ባለቤት ነው። እነዚህን ኮከብ አትሌቶች ጨምሮ ሌሎች በርካታ የርቀቱ ጠንካራ አትሌቶች በዘንድሮው ለንደን ማራቶን ተሳታፊ መሆናቸውን ተከትሎ ውድድሩ ከወዲሁ በጉጉት እየተጠበቀ ነው። ‹‹ያለፈው ዓመት ውድድር በተለይም በወንዶች የምንጊዜውም ምርጡ ነበር›› ያለው የኢሊት አትሌቶች ኃላፊ ስፔንሰር ባርደን የዘንድሮው የተሻለ እንደሚሆን ያለውን እምነት ገልጿል። በአምናው ውድድር ሞስነትና ሙሌ ኬንያዊውን ድንቅ አትሌት እስከ አርባ ኪሎ ሜትር ድረስ የፈተኑበት መንገድ ከዚህ ቀደም እንዳልገጠመው የተናገረው ባርደን ዘንድሮ እነዚህ አትሌቶች በተሻለ የራስ መተማመን ሊያሸንፉ የሚችሉበት ዕድል እንዳለ አብራርቷል። ከሦስት ወራት በፊት በቬና ማራቶን አርባ ሁለት ኪሎ ሜትርን ከ2፡00 ሰዓት በታች በማጠናቀቅ የመጀመሪያው የዓለማችን አትሌት የሆነው ኪፕቾጌ ዘንድሮ በለንደን ማራቶን ማሸነፍ ከቻለ አምስት ጊዜ ያሸነፈ ብቸኛው አትሌት በመሆን ተጨማሪ ታሪክ ያኖራል። በዘንድሮው ውድድር የ2017 የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ አሸናፊው ታምራት ቶላን ጨምሮ ኬንያዊው ማሪየስ ኪፕሴሬምና ኖርዌያዊው ሶንድሬ ኖርድስታድ ተፎካካሪ መሆናቸው እንደተረጋገጠ አትሌቲክስ ዊክሊ አስነብቧል። በሴቶች መካከል በሚካሄደው ፉክክርም የዓለም ክብረወሰን ባለቤቷና ያለፈው ዓመት የለንደን ማራቶን አሸናፊዋ ኬንያዊት ብሪጊድ ኮስጌ ከትናንት በስቲያ ተሳታፊ መሆኗን ያረጋገጠች ሲሆን በቀጣይ ጊዜዎች ሌሎቹ ተሳታፊዎች ይፋ እንደሚደረጉ ይጠበቃል። አዲስ ዘመን ጥር 7/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=25696
[ { "passage": "የጽናት ምልክቱና በ10ሺ ሜትር ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ኢትዮጵያን ወክሎ የዓለም ምርጡ አትሌት ሲሰኝ የመጀመሪያው ነው። በአቴንሱ የዓለም ቻምፒዮና 10ሺ ሜትር እንዲሁም በፈረንሳይ የቤት ውስጥ ቻምፒዮና 3ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያ በማጥለቅ አገሩን ባስጠራ ማግስት፣ የጎልደን ሊጉ አሸናፊም በሆነበት ዓመት እአአ 1998 የዓመቱ የዓለም ምርጥ አትሌት በሚል ለመሸለም በቃ። በኃይሌ እግር የተተካው ቀነኒሳ በቀለ ደግሞ ይህንን ክብር በማግኘት ሁለተኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ለመሰኘት ቻለ። የ5ሺ፣ 10ሺ እና የአገር አቋራጭ ንጉሱ በተከታታይ እአአ በ2004 እና 2005 በወንዶች የዓለም ምርጥ አትሌት በመሆንም ታሪካዊ አትሌትነቱን አስመስክሯል። በወንዶች በኩል ከቀነኒሳ ቀጥሎ ይህንን ክብር ያገኘ ኢትዮጵያዊ አትሌት ባይኖርም በሴቶች በኩል ግን እስከ ቅርብ ዓመታት ለማሸነፍ የቻሉ አትሌቶች ታይተዋል። አትሌት መሰረት ደፋር እአአ በ2007 ይህንን ሽልማት ያሳካች አትሌት ናት። ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታት ባይቆጠርም እአአ በ2015 ገንዘቤ ዲባባ ሁለተኛውን ክብር እንዲሁም በረጅም ርቀት የዓለም እና የኦሊምፒክ ቻምፒዮናዋ አልማዝ አያና በ2016 የዓመቱ ምርጥ አትሌት በመባል ለመሸለም በቅተዋል። በዓለም ላይ በተለይ በረጅም ርቀት አትሌቲክስ ተጽእኖ ፈጣሪ ከሚባሉ አገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያናት። በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ዕውቅና በተሰጣቸው ውድድሮች ላይ በግላቸው ከሚሳተፉት አትሌቶች ባሻገር በዳይመንድ ሊግ፣ ዓለም ቻምፒዮና አንዲሁም በኦሊምፒክ መድረክም ሜዳሊያ ያጠለቁ የዝነኛ አትሌቶች ምድርም ናት፤ ኢትዮጵያ። አሸንፎ ሜዳሊያውን ማጥለቅ ብቻም ሳይሆን ሰዓት በማሻሻልና የዓለም ክብረወሰንን በመስበር ጭምር በርካታ ስኬታማ አትሌቶችን ለዓለም አበርክታለች። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዓለም ምርጥ አትሌቶች ሽልማት ማሸነፍ ባይችሉ እንኳን ከመጀመሪያዎቹ አስር እጩዎች በሁለቱም ፆታ መካተታቸው ብርቅ አልነበረም። ባለፈው ዓመትና ዘንድሮ ግን በተከታታይ ከአስሩ እጩዎች ዝርዝር ውስጥ ሳይካተቱ ቀርተዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባለሙያዎች እንዲሁም ከሁሉም አህጉራት በተወጣጡ ተወካዮች በሁለቱም ጾታ በዓመቱ ጥሩ ብቃት ያሳዩ 20 አትሌቶች ቀርበዋል። ዕጩዎቹም በዳይመንድ ሊግ፣ በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና፣ በዶሃው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና እንዲሁም ማህበሩ በሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ላይ በሩጫ፣ ዝላይ እና ውርወራ የተሻለ ብቃት ያሳዩ ሲሆኑ ከነዚህ መካከል ለተከታታይ ሁለት ዓመታት አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት ሳይካተት መቅረቱ አስገራሚ ሆኗል። ዘንድሮ እጩ ሆነው ከቀረቡት አትሌቶች መካከል አሜሪካ በርካታ አትሌቶችን በማስመረጥ ቀዳሚዋ አገር ሆናለች። በዓመቱ ከተካፈለባቸው አምስት የ800 ሜትር ውድድሮች አራቱን ያሸነፈው ዶናቫን ብራዜር በእጩነት ከቀረቡት መካከል ይገኛል። አሜሪካዊው አትሌት በቻምፒዮናው ላይ በ800 ሜትር 1:42.34 የዓለም ክብረወሰን የሆነ ሰዓት ከማስመዝገቡም ባሻገር የዳይመንድ ሊጉ አሸናፊ ነው። በዓመቱ በ100 ሜትር ውድድር ተዕእኖ ፈጣሪ የነበረውና የዶሃ ርቀቱን 9 ሰከንድ ከ76 ማይክሮ የገባው ክርስቲያን ኮለመንም ሌላኛው እጩ ነው። የከፍታ ዝላይ አሸናፊው ሳም ኬንድሪክስ፣ የ200 ሜትር ሯጩ ናህ ላይለስ እንዲሁም የርዝመት ዘላዩ ክርስቲያን ቴይለር በእጩነት የቀረቡ አሜሪካዊያን አትሌቶች ናቸው። ባለፈው ሳምንት ማራቶንን ለመጀመሪያ ጊዜ ከሁለት ሰዓት በታች በመግባት ታሪክ ያጻፈው ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌም በእጩነቱ ተካቷል። አትሌቱ ዕውቅና የሌለውን የስፖርት ትጥቅ አምራቹን ኩባንያ ናይኪ ፕሮጀክት የሆነውን ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች የማጠናቀቅ ህልም ከማሳካቱም ባለፈ በለንደን ማራቶን\n2:02:37 በመግባት የራሱን ፈጣን ሰዓት በማሻሻል የዓለም ክብረወሰኑን አለማስነጠቁ የሚታወቅ ነው። የአገሩ ልጅ የሆነው ቲሞዚ ቺሩዪት ሌላኛው እጩ ሲሆን፤ በ1ሺ500ሜትር የዳይመንድ ሊግ እንዲሁም የዓለም ቻምፒዮን ነው። በአውሩስ በተካሄደው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮን የሆነው ኡጋንዳዊው ጆሹዋ ቼፕቴጊም ከእጩዎቹ ተካቷል። አትሌቱ በ10ሺ ሜትር ቀዳሚ የሆነውን\n26:48.36 ሰዓት ሲያስመዘግብ በ500ሜትር የዳይመንድ ሊጉ ቻምፒዮን ነው። የ400ሜትር አትሌቱ ባህሬናዊ ስቲቭ ጋርድነር፣ በዲስከስ ውርወራ የዓለም ቻምፒዮኑ ስዊድናዊ ዳንኤል ስታል እንዲሁም ኖርዌያዊው ካርስቴን ዋርሆልም በምርጫው የተካተቱ ሌሎች እጩዎች ናቸው። ለምርጫው የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ባለሙያዎች 50 በመቶ የሚሆነውን ድምጽ የሚሰጡ ሲሆን 25 በመቶ የሚሆነውን ደግሞ ሌላው ህዝብ በድረገጾች ድምጹን የሚሰጥ ይሆናል። እጩዎቹን አሸናፊ ለማድረግም በየትኛውም የህዝብ መገናኛ እንዲሁም የማህበራዊ ገጾች ማስተዋወቅ የሚረዳቸው ሲሆን፤ ከወር በኋላ የመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ይታወቃሉ። አሸናፊው እትሌትም በሞናኮ በሚኖረው ስነስርዓት ላይ ይፋ እንደሚደረግ ይታወቃል። አዲስ ዘመን  ረቡዕ ጥቅምት 5/2012ብርሃን ፈይሳ ", "passage_id": "ef65a2e4a53ad1e23e40e84560b36c18" }, { "passage": "በፖርትላንዱ የዓለም አዳራሽ ውስጥ ሻምፒዮና ውድድር በሴቶቹ 3,000 ሜትር ውድድር አሸናፊዋ ልማደኛዋ ገንዘቤ ዲባባ እንደምትሆን ሳይታለም የተፈታ ነበር።​በተመሳሳይ ርቀት የወንዶቹን ድል የተቀዳጀው ደግሞ ወጣት ዮሚፍ ቀጄልቻ ነው። ሁለቱም በየግላቸው ያስመዘገቧቸው ሰዓቶችም የሚናቁ አልሆኑም፥ የገንዘቤ 8 ደቂቃ ከ 47 ነጥብ4 - 3 ሴኮንድ ሲሆን የዮሚፍ 7 ደቂቃ ከ 57 ነጥብ 2 - 1 ሴኮንድ ሆኗል።ሁለቱም የኢትዮጵያ አትሌቶች በመጪው ግንቦት ዩጂን ኦሪጎን በሚካሄደው የዳያመንድ ሊግውድድር ለመሳተፍ ተመልሰው እንደሚመጡ ይጠበቃል።ኤዲ ኢዛርድ የተባለ የ 54 ዓመት ኮሜዲያን፥ 27 ማራቶኖችን በ 27 ቀናት ውስጥ ሮጧል።አርቲስቱ ይህን ያደረገው ኔልሰን ማንዴላ የመጀመሪያው የደቡብ አፍሪካ ጥቁር ፕሬዘዳንትከመሆናቸው በፊት ለ 27 ዓመታት በእሥር መቆየታቸውን ለማስታወስ ነው ተብሏል።አስቂኙ አርቲስት በጠቅላላው የሮጠው 707 ማይሎችን ሲሆን በውሃ ጥም ማረሩና ቆዳው መቆሳሰሉተስተውሏል። ኤዲ ኢዛርድ አጋጣሚውን የስፖርት ፕሮግራሞችን ለማስፋፊያ ገንዘብ ማሰባሰቢያነትም ተጠቅሞበታል።በእለቱም ከደጋፊዎቹ ከአንድ ሚሊዮን ፓውንድ በላይ መሰብሰብ ችሏል። ሰሎሞን ክፍሌ ዝርዝሩን አጠናቅሮ አቅርቦታል፣ ከዚህ በታች ካለው የድምጽ ፋይል በመጫን ያድምጡ። ", "passage_id": "fdf4a3cca18ab20bc8cc7c655e95ddd8" }, { "passage": "ከተያዘው ሳምንት ጀምሮ ስሙን የዓለም አትሌቲክስ በሚል የቀየረው የስፖርቱ የበላይ አካል ዓመታዊው የምርጥ አትሌቶች ምርጫውን ሊያካሂድ ቀናት ብቻ ቀርተውታል፡፡ ስፖርት ወዳዱ ህብረተሰብ እንዲሁም የአትሌቶቹ የቅርብ ሰዎች በኢሜይል እንዲሁም በማህበራዊ ድረገጾች በተዘጋጁት ድምጽ መስጫዎች ይገባዋል ለሚሉት አትሌት ይሁንታቸውን ሰጥተዋል፡፡ በእስካሁኑ 25 ከመቶ ድርሻ ባለው የህዝብ ድምጽ እና ባለሙያዎች ባደረጉት ምርጫ መሰረትም የመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ታውቀዋል፡፡በዚህም መሰረት ባለፈው የውድድር ዓመት ብቃታቸው እንዲሁም በቅርቡ በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ባገኙት ውጤት መሰረት ከአምስት ሃገራት አምስት የተለያዩ ሴት አትሌቶች ለመጨረሻው ዙር በቅተዋል፡፡ በመካከለኛ ርቀት ኔዘርላንዳዊቷ ሲፈን ሃሰን ከዓመቱ ምርጥ አትሌቶች መካከል ተገኝታለች፡፡ አትሌቷ በአበረታች ቅመሞች ምክንያት በምርመራ ላይ ከሚገኙት አሰልጣኟ አልቤርቶ ሳላዛር ጋር በተያያዘ በጥርጣሬ ትታይ እንጂ በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በ1ሺ500 እና10ሺ ሜትር አሸናፊ መሆኗ በእጩነት ሊያስመርጣት ችሏል። ይህም ብቻ ሳይሆን የ 1ሺ500 እና 5ሺ ሜትር  የዳይመንድ ሊግ የድርብ ድል ባለቤቷ ሲፈን በማይል ውድድርም 4:12.33 የሆነ የዓለም ክብረወሰንን በሞናኮ አስመዝግባለች። ይህ በአመቱ ያስመዘገበችው ስኬትም አትሌቷን ከዘጠኝ ቀናት በኋላ በሞናኮ በሚኖረው ስነስርዓት የዓለም ምርጥ ሴት አትሌት በመባል የክብሩ ባለቤት እንድትሆን ይረዳታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የአጭር ርቀት ተወዳዳሪዋ ጃማይካዊት አትሌት ሼሊ-አን ፍራዘር-ፕረይሲም በዓመቱ በተካፈለችባቸው ውድድሮች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ለሽልማቱ አሳጭቷታል። አትሌቷ በዶሃው ቻምፒዮና በተካፈለችባቸው የ100 ሜትር እና 4በ400 ሜትር ውድድሮች 10 ሰከንድ ከ71 ማይክሮ ሰከንድ እና 41 ሰከንድ ከ44 ማይክሮ ሰከንድ የሆነ ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ነበረች። የ32 ዓመቷ ፕረይሲ በአሜሪካ አህጉር በሚዘጋጀው ውድድር የ200 ሜትር አሸናፊም ነበረች፡፡ የዓለም ፈጣኗ ሴት አትሌት በአመቱ ከተሳተፈችባቸው አስር ውድድሮች በሰባቱ ቀድማ በመግባት ብርቱ አትሌትነቷን አስመስክራለች፡፡ የሰው ልጅ ማራቶንን ከአንድ ሰዓት በታች መግባት እንደሚችል የሃገራ ልጅ በሙከራ ውድድር ባስመሰከረበት ማግስት የዓለም ሴቶች የማራቶን ክብረወሰንን የሰበረችው ኬንያዊት አትሌት ብርጊድ ኮስጊም ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች መካከል ተገኝታለች፡፡ በቺካጎ ማራቶን ለ16 ዓመታት የቆየውን ክብረወሰን 2:14:04 በሆነ ሰዓት በመግባት የሰባበረችው አትሌቷ የለንደን ማራቶን አሸናፊም ነበረች፡፡ ወጣቷ አትሌት በዓመቱ በተሳተፈችበት የግማሽ ማራቶን ውድድርም 1:04:28 የሆነ ፈጣን ሰዓት አላት። ሌላኛዋ እጩ አሜሪካዊቷ ደሊላ ሙሃመድ በዓመቱ በ400 ሜትር ያሳየችው አቋም ሊያስመርጣት ችሏል፡፡ አትሌቷ በሃገር አቀፍ ቻምፒዮና 52 ሰከንድ ከ20 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ቀዳሚዋ ስትሆን፤ በ400 ሜትር መሰናክል በራሷ የተያዘውን ክብረወሰን 52 ሰከንድ ከ16 ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ብቃቷን አስመስክራለች፡፡ በ4 በ400 ሜትርም በተመሳሳይ የዓለም ቻምፒዮን ናት፡፡ በርዝመት ዝላይ ቬንዙዌላዊቷ ዩሊማር ሮጃስ ለመጨረሻው ዙር መብቃት ችላለች፡፡ አትሌቷ 15.37 ሜትር በመዝለል የዓለም ቻምፒዮን ስትሆን፤ ከዚህ ቀደም የዘለለችው 15.41 ሜትር ደግሞ ከዓለም የምንጊዜም ቀዳሚዎቹ መካከል ሊሰፍርላት ችሏል፡፡ ሮጃስ አህጉር አቀፍ ውድድርን ጨምሮ ከተካፈለችባቸው 12 ውድድሮች ዘጠኝ በሚሆኑት ላይ አሸናፊ መሆኗ ከዓለም ምርጦች ተርታ ያሰልፋታል የሚል ግምት አግኝታለች፡፡አዲስ ዘመን ጥቅም4/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "85f47c0c1d60fc34dafa3b55711aa596" }, { "passage": " በስፖርት የመጨረሻውን ደረጃ ክብር የሚያስገኘው ውድድር ኦሊምፒክ መሆኑ ይታወቃል። በዓለም ትልልቅ ስም ያላቸው ዝነኛ አትሌቶች ሃገራቸውን ወክለው የሚሳተፉበት እንዲሁም በርካታ ክብረወሰኖች የሚሰባበሩበትም ነው። በመሆኑም በአትሌቶች ዘንድ በመድረኩ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ብቻም ሳይሆን ተሳትፎውም ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው።ኦሊምፒክ በየአራት ዓመቱ ስለሚካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት የሚደረግበት ሲሆን፤ ወጥ አቋም የሌላቸው አትሌቶች በተደጋጋሚ ኦሊምፒክ ላይ ሊታዩ አይችሉም። በመሆኑም በርካታ ተሳትፎ ያላቸው አትሌቶችን ለማግኘት አዳጋች ነው። እንግሊዛዊቷ አትሌት ግን በመጪው ዓመት ስድስተኛ የኦሊምፒክ ተሳትፎዋን ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኗን ነው ያሳወቀችው። በተለይ ለወጣት አትሌቶች አስተማሪ የሆነ ተሞክሮዋንም ለቢቢሲ አጋርታለች።ጆ ፓቬ አምስት አሊምፒኮች ላይ የተሳተፈች አንጋፋ አትሌት ስትሆን በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስድስተኛ ተሳትፎዋን በማድረግ የክብረወሰን ባለቤት ለመሆን ፍላጎት አላት። ከዚህ ቀደም የሃገሯ ልጅ የሆነችው ጦር ወርዋሪ ቴሳ ሳንደርሰን ስድስት ኦሊምፒኮች ላይ ሀገሯን የወከለች አትሌት በመባል ተመዝግባለች። ፓቬ ስድስተኛዋን ተሳትፎ የምታደርግ ከሆነ ደግሞ በመም አትሌት የመጀመሪያዋ ትሆናለች።\nፓቬ እአአ በ2014 ከወሊድ በኋላ በአውሮፓ ሻምፒዮና በ10ሺ ሜትር ስትሳተፍ በአንጋፋነቷ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆና ነበር። ይሁን እንጂ በ40ዓመቷ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆን ብቃቷን ማስመስከር ችላለች። በቶኪዮው ኦሊምፒክ ስትሳተፍም ዕድሜዋ 46 ስለሚሆን ምናልባትም በኦሊምፒኩ አንጋፋዋ አትሌት ልትሆን ትችላለች። ፓቬ ለቢቢሲ በሰጠችው አስተያየት ላይም «ዕድሜዬን ረስቼ ስድስተኛውን የኦሊምፒክ ተሳትፎዬን አደርጋለሁ» ብላለች።አትሌቷ ሃገሯን ወክላ በኦሊምፒክ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው እአአ በ2ሺ በተካሄደው የሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ ነበር። «በቶኪዮ የሚካፈለው ብሄራዊ ቡድን ጥሩ ተፎካካሪ እንዲሆን እፈል ጋለሁ። በመሆኑም ዝግጅታችንን ቀድመን መጀመር ይገባናል፤ ፉክክሩ ደግሞ ይበልጥ ደስ የሚያሰኝ ነው» ብላለች። የሁለት ልጆች እናት የሆነችው አትሌቷ ከኦሊምፒኩ አስቀድሞ በዘንድሮው የዶሃ ዓለም ሻምፒዮና አቅሟን የመፈተሽ ፍላጎት እንዳላትም ጨምራ ገልጻለች። እአአ በ2017 በለንደን በተካሄዱት ሁለት ትልልቅ የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ ብትሆንም አልተሳካላትም ነበር። በለንደን ማራቶን ውድድሯን ሳታጠናቅቅ አጋማሽ ላይ ስታቋርጥ፤ በ10ሺ ሜትር በተካፈለችበት ሻምፒዮና ደግሞ በጉዳት ምክንያት ውድድሯን ለማጠናቀቅ አልቻለችም ነበር።ያለፈው ዓመት በተካሄደ ሌላ ውድድር ግን በረጅም ርቀት የመም ላይ ውድድር ሶስተኛ በመሆን የነሃስ ሜዳሊያውን ወስዳለች። በባለቤቷ የምትሰለጥነው አትሌቷ በልምምድ ቦታዎች ላይም ነፍስ ያላወቁ ልጆቿን ይዛ ትሄዳለች «ሩጫ እወዳለሁ፤ የአእምሮ እና ሰውነት ጤናን ለማግኘት ያግዛል። ከቤተሰብህ ጋር ሆነህ ስትከውን ደግሞ ይበልጥ መነሳሳትን ይፈጥራል። ባለቤቴ ያግዘኛል፤ ሥራችንን የምንሰራውም እንደ ቡድን ነው። ሯጭ ስትሆን መጨናነቅን ማስወገድ የግድ ነው ይህም የአእምሮን ጤና ይሰጣል። እድሜህንም እንደ ልምድ መጠቀም ትጀምራለህ» ስትልም የህይወት ልምዷን ታጋራለች።የአትሌቷ የኦሊምፒክ ተሳትፎ በተለያዩ ችግሮች የታጀበ ይሁን እንጂ ተስፋ አለመቁረጧ ግን ለብዙዎች ተሞክሮ የሚሆን ነው። እአአ 1997 ከባድ የሆነና ውስብስብ ቀዶ ጥገና የሚያስፈልገው የጉልበት ጉዳት የደረሰባት ቢሆንም፤ ከዚያ አገግማ በሲድኒ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። እአአ በ2004ቱ የአቴንስ ኦሊምፒክ ከመሳተፏ ሶስት ወራት በፊት የጡንቻ ጉዳት ቢደርስባትም አምስተኛ ደረጃ በመያዝ የዲፕሎማ ተሸላሚ ነበረች።በ2008ቱ የቤጂንግ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሯን ያጠናቀቀችው ደግሞ በውድድሩ ዋዜማ በምግብ መበከል የጤና መታወክ ስለደረሰባት ነበር። በሀገሯ በተዘጋጀው የ2012 ኦሊምፒክ በ5 እና 10ሺ ሜትር ውድድሮች ተሳትፎዋ ሰባተኛ ደረጃ በመያዝም የመጀመሪያዋ አውሮፓዊት አትሌት ተሰኝታለች። በሪዮ በተካሄደው የ2016ቱ ኦሊምፒክ ደግሞ ዘግይታ ውድድሩን በመጀመሯ በ10ሺ ሜትር 15ኛ ደረጃን ነበር የያዘችው። «የሪዮ ኦሊምፒክ ተሳትፎዬ በጣም አስደሳች ነበር፤ አብረውኝ የሮጡት አትሌቶችም ከእኔ በ20ዓመት የሚያንሱ ነበሩ። ቢሆንም ሁሌም ሃገሬን መወከል ለእኔ ኩራት ነው» ስትልም ትገልጻለች።አዲስ ዘመን ጥር 13/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "121a3477a1e1f36d985d4b50ab4afece" }, { "passage": "የዓለም አትሌቲክስ በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ሽልማት በሞናኮ ሊካሄድ ዛሬ አስራ አንድ ቀን ብቻ ይቀረዋል። ለሁለት ተከታታይ ዓመታት በሁለቱም ፆታ አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት ከመጀመሪያዎቹ አስር እጩዎች ውስጥ እንኳን መካተት እንዳልቻለ ይታወሳል። በተመሳሳይ ወጣትና ተስፈኛ የሆኑ ከሃያ ዓመት በታች ያሉ አትሌቶች በሚወዳደሩበት ሽልማት ዘርፍ ሁለት ወንዶችና አንድ ሴት ኢትዮጵያዊት አትሌት ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ውስጥ መካተታቸው ይታወቃል። የዓለም አትሌቲክስ ትናንት ከሰዓት በኋላ በዘንድሮው ዓመት በወንዶች የመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች ዝርዝር ይፋ አድርጓል። የመጨረሻዎቹ ሴት እጩዎችም ዛሬ የሚለዩ ይሆናል። ጆሹአ ቺፕቴጌ ባለፈው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአስር ሺ ሜትር ቻምፒዮን የሆነው ዩጋንዳዊው ጆሹአ ቺፕቴጌ የመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች መቀላቀል የቻለ ሲሆን አትሌቱ በ2019 የውድድር ዓመት ያሳየው አስደናቂ ብቃት ሽልማቱን የማሸነፍ እድል እንዳለውም አመላካች ነው። ጆሹአ አርሁስ በተካሄደው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ በውድድር ዓመቱ ትኩረት የተሰጠው አትሌት ሆኗል። ባልተጠበቀ መልኩም ጠንካራዎቹን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዳይመንድ ሊግ በማሸነፍ በአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ አሸናፊ ለመሆን በቅቷል። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮናም 26፡48፡36 የሆነ መሪ ሰዓት አስመዝግቦ በውድድር ዓመቱ ለታላቅ ስኬት እጩ መሆን ችሏል። ሳም ኬንድሪክስ አሜሪካዊው ምርኩዝ ዘላይ ሳም ኬንድሪክስ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው አስራ ሰባት ከቤት ውጪ ውድድሮች አስራ ሁለቱን በድል አጠናቋል። የውድድር ዓመቱ የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ከመሆኑ ባሻገር የዓለም ምርኩዝ ዝላይ ቻምፒዮን ነው። በአሜሪካ የምርኩዝ ዝላይ ቻምፒዮና 6 ነጥብ 06 ሜትር በመዝለል ያስመዘገበው ስኬት ለዓለም ምርጥ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻ እጩነት አብቅቶታል። ኢሉድ ኪፕቾጌ ያለፈው ዓመት የሽልማቱ አሸናፊ የሆነው ኬንያዊው የማራቶን ፈርጥ ኢሉድ ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ ሁለት ፉክክሮች ላይ ብቻ ቢታይም ያስመዘገበው ታሪክ ለመጨረሻ እጩነት አብቅቶታል። ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ የለንደን ማራቶንን ክብረወሰን በማሻሻል በ2፡02፡37 ሰዓት ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ከዚህ በላይ ግን ከወር በፊት በቬና ማራቶን የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ያሳየበት ውድድር አይዘነጋም። ኪፕቾጌ ከትጥቅ አምራች ኩባንያው ናይኪ ጋር በመሆን በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ታግዞም ቢሆን ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች ማጠናቀቅ እንደሚቻል አስመስክሯል። 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማራቶንን በማጠናቀቅ በታሪክ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆን ቢበቃም የተመዘገበው ሰዓት በዓለም ክብረወሰንነት እንዳልተያዘ ይታወሳል። ኖህ ላይልስ አሜሪካዊው የአጭር ርቀት አትሌት ኖህ ላይልስ የሁለት መቶና አራት በአራት መቶ ሜትር ዱላ ቅብብል ቻምፒዮን ነው። በሉዛን ዳይመንድ ሊግ ሁለት መቶ ሜትርን 19፡50 በሆነ ሰከንድ በማጠናቀቅ በታሪክ አራተኛው ፈጣን ሰዓት ባለቤት መሆኑም አይዘነጋም። የዳይመንድ ሊግ የመቶና ሁለት መቶ ሜትር አጠቃላይ አሸናፊ መሆኑም በመጨረሻዎቹ እጩዎች ዝርዝር ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። ካርልስተን ዋርሆልም ኖርዌያዊው የአጭር ርቀት ኮከብ አትሌት ካርልስተን ዋርሆልም በአራት መቶ ሜትር መሰናክል የዓለም ቻምፒዮን ነው። ይህ አትሌት በውድድር ዓመቱ በተለያዩ ርቀቶች በቤት ውስጥም ሆነ ከቤት ውጪ ውድድሮች ሽንፈት አልገጠመውም። ዳይመንድ ሊግን ጨምሮ የአውሮፓ ቻምፒዮን ሲሆን ያስመዘገበው 46፡92 በታሪክ ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ሆኗል። ይህም ስኬቱ ምናልባትም ከዩጋንዳዊው አትሌት ጋር ሽልማቱን ለማሸነፍ ጠንካራ ተፎካካሪ ያደርገዋል ተብሎ ይጠበቃል። አዲስ ዘመን ኅዳር\n2 /2012   ቦጋለ አበበ", "passage_id": "7a2be52d0f1ba4d19993aa253c06ffd2" } ]
a021c2fd7d4e693fae9052d88d7a3e37
5e8120159b7139f47cfec0b71a66854d
የሠራተኞች የበጋ ወራት ውድድር እሁድ ይጀመራል
 ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚሰራበትና በሚማርበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በማዘውተር ጤናማ እንዲሆን የስፖርት ፖሊሲው ይደነግጋል። ሰራተኛው ማህበረሰብ በብዙ ተቋማት በሚሰራበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በስፋት ሲሳተፍ ባይስተዋልም ዓመታዊ የሰራተኞች ስፖርት ውድድሮች ላይ ሲሳተፍ ይታያል። ይህም የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን(ኢሠማኮ)በዓመት የተለያዩ መርሃ ግብሮች የሚያከናውናቸው የስፖርት መድረኮች ናቸው። ከነዚህ የኢሠማኮ የስፖርት መድረኮች ትልቅ ትኩረት የሚሰጠውም ዓመታዊው የሰራተኞች የበጋ ወራት የስፖርት ውድድር በጉልህ ተጠቃሽ ሲሆን ከታኅሣሥ ወር አንስቶ እስከ ግንቦት መጨረሻ የሚዘልቅ ነው፡፡ የሰራተኞች የበጋ ወራት የስፖርት ውድድር በአገራችን ስፖርት ታሪክ መካሄድ ከጀመረ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረና አንጋፋ ከመሆኑ ባሻገር አገርን ወክለው የመካከለኛና ምስራቅ አፍሪካ(ሴካፋ) ዋንጫን ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች መሳተፍ የቻሉ ስፖርተኞችን ያፈራ ስለመሆኑ ይነገራል።ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በስፋት የተለያዩ ማህበራትን እያሳተፈ የሚገኘው ይህ ውድድር የመገናኛ ብዙሃን ትኩረትን ከመሳብ ባሻገር በአገራችን ከሚከናወኑ ታላላቅ የስፖርት መድረኮች አንዱ እየሆነ ይገኛል፡፡ በዚህም አዳዲስ ተሳታፊ ማህበራትን ወደ ውድድር ከመሳብ በዘለለ ቀድሞ ዝነኛ ተፎካካሪ የነበሩና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከውድድሩ የራቁ ማህበራትን ወደ ውድድር እየመለሰ ይገኛል።የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ ስቴድየም በሚጀመረው የበጋ ወራት ውድድርም አርባ አዳዲስና ነባር የሰራተኛ የስፖርት ማህበራት ተሳታፊ ለመሆን ዝግጅታቸውን እንደጨረሱ የኢሠማኮ የስፖርት ክፍል ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ካሳ ለዝግጅት ክፍላችን ተናግረዋል፡፡ በሁለት ዲቪዚዮን ተከፍሎ በሚካሄደው የእግር ኳስ ውድድር ከሰላሳ ማህበራት የተውጣጡ 750 ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ይሆናል፡፡ በሴቶች ቮሊቦል ውድድር ከአስራ አምስት ማህበራት 253 ተወዳዳሪዎች ሲሳተፉ በወንዶች ከአስር ማህበራት 150 ተወዳዳሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡ በሴቶች ቼስ ውድድር ከአምስት ማህበራት 25፣ በወንዶች ከአስር ማህበራት 50 ተወዳዳሪዎች ይሳተፋሉ፡፡ በጠረጴዛ ቴኒስ ወንዶች ከአስር ማህበራት 50 ተሳታፊዎች፣ በሴቶች ደግሞ ከዘጠኝ ማህበራት 45 ተሳታፊዎች ይወዳደራሉ፡፡ በወንዶች ዳርት ውድድር ከአስራ ሁለት ማህበራት 60 ተሳታፊዎች፣ በሴቶች ከስምንት ማህበራት 40 ተሳታፊዎች ይፎካከራሉ፡፡ በከረንቦላ ውድድር ከአስራ ሁለት ማህበራት የተውጣጡ 60 ተወዳዳሪዎች፣ በገበጣ ውድድር ከአስር ማህበራት 50 ተወዳዳሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡ በአትሌቲክስ ወንዶች ከስምንት ማህበራት 144 ተወዳዳሪዎች፣ በሴቶች ከሰባት ማህበራት 126 ተወዳዳሪዎች ተፎካካሪ ይሆናሉ፡፡ አዝናኝ በሆነው የገመድ ጉተታ ውድድር በወንዶች ከአምስት ማህበራት 75 ተፎካካሪዎችና በሴቶች ከሦስት ማህበራት 45 ተወዳዳሪዎች ተካፋይ ይሆናሉ፡፡ በአጠቃላይ በውድድሩ 1945 የሰራተኛ ስፖርት ማህበራት ተወዳዳሪዎች ተካፋይ ሲሆኑ 605 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን አቶ ዮሴፍ ገልፀዋል፡፡ ውድድሩ እሁድ ሲጀመርም ጠንካራ ፉክክር በሚደረግበት እግር ኳስ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ከኢስት አፍሪካን ቦትሊንግ ሼር ካምፓኒ(ኮካ ኮላ) ጋር የመክፈቻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ የሴቶች አራት መቶ ሜትርና የወንዶች አንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የአትሌቲክ ውድድሮችም በውድድሩ መክፈቻ እለት ይከናወናሉ።የገመድ ጉተታና እን ቁላል በማንኪያ ይዞ የመሮጥ አዝናኝ ውድድሮችም በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ተካተዋል፡፡  አዲስ ዘመን ታኀሣሥ 16 / 2012   ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=24726
[ { "passage": "ሰባተኛው መላው የአማራ ክልል ስፖርታዊ ውድድር በሰሜን ወሎ ዞን ወልድያ ከተማ አስተዳደር ይደረጋል፡፡ ስፖርታዊ ውድድሩ የሚካሄደው ‹‹ስፖርታዊ ጨዋነትን ማስፈን የሁሉም ስፖርት ወዳድ ኃላፊነት ነው›› በሚል መሪ ሐሳብ ነው፡፡ በየሁለት ዓመታት ልዩነት የሚደረገው የመላው የአማራ ክልል ስፖርታዊ ውድድር ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ ሲቀጥል ከሦስት ሺህ በላይ ስፖርተኞች ይታደሙበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ስፖርታዊ ውድድሩን ለማዘጋጀት የተደረገውን ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ ለአብመድ መረጃ የሰጡት የሰሜን ወሎ ዞን ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ሙላት ዓለሙ “ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቀን እንግዶቻችንን የመቀበል ሥራ ብቻ ይቀረናል” ብለዋል፡፡ስፖርታዊ ውድድሩ በሠላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላትና ከኅብረተሰቡ ጋር ቅንጅት እንደተፈጠረም ገልጸዋል፡፡ ስፖርቱ የክልሉን ሕዝቦች በአንድ ላይ የሚያገናኝ ስለሆነ ለከተማዋ መልካም አጋጣሚ በመሆኑ ለውድድሩ የሚሆን በቂ ዝግጅት መደረጉን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡በአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያው አቶ አብዮት መኩሪያው መላው የአማራ ክልል ስፖርታዊ ውድድር ከየካቲት 24 እስከ መጋቢት 8/2012 ዓ.ም እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡ በውድድሩ ሁሉም ዞኖች፣ ብሔረሰብ አስተዳደሮችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የስፖርት ልዑካን ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አቶ አብዮት ተናግረዋል፡፡ውድድሩ በ20 የስፖርት ዓይነቶች ይካሄዳል፡፡ የውኃ ዋና ስፖርት በኮምቦልቻ፣ የባድሜንተን ስፖርት ደግሞ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደሮች ሲካሄዱ ቀሪ 18 የውድድር ዓይነቶች በወልድያ ከተማ እንደሚካሄዱ ታውቋል፡፡ በየሁለት ዓመታት ልዩነት የሚካሄደው የመላው አማራ ክልል ስፖርታዊ ውድድር የክልሉን ሕዝቦች በአንድ መድረክ በማገናኘት፣ የተሻሉ ተወዳደሪዎችን ለማስመረጥ፣ የተጫዋቾችን ብቃት ለመፈተሽና የዞንና የከተማ አስተዳደሮችን ዝግጅት ለመገምገም ያለመ ነው ተብሏል፡፡ዘጋቢ፡-ታርቆ ክንዴ", "passage_id": "745abb79e3c91a8f03fbb1ea31e98e80" }, { "passage": "የኢትየጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በበላይነት የሚመራቸው የሊግ ውድድሮች ከመጀመራቸው በፊት የ2009 የውድድር ዘመን ግምገማ ፣ ስለ ቀጣይ አመት የሊጎቹ የአደረጃጀት (ፎርማት) ሁኔታ እና ደንቦች ላይ ጨምሮ የእጣ ማውጣት ስነስርዓቱን የሚያደርግበትን ቀን እና ቦታ ይፋ አድርጓል።የወንዶች ፕሪምየር ሊግ መስከረም 15 እንዲሁም የሴቶቹ ፕሪምየር ሊግ በማግስቱ መስከረም 16 ሀዋሳ ላይ እንደሚደረግ ሲገለፅ የከፍተኛ ሊጉ እና የአንደኛ ሊጉ ደግሞ መስከረም 21 እና መስከረም 27 አዲስ አበባ ላይ እንደሚደረግ ለማወቅ ተችሏል። ከ20ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ ጥቅምት 15 ፣ ከ17ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ ጥቅምት 20 አዲስ አበባ ላይ እንደሚደረግ ፌደሬሽኑ ለሶከር ኢትዮጰያ ገልጿል።ከዚህ ቀደም ስድስቱም የሊግ ውድድሮች የሚጀመሩበት ቀን ይፋ መሆኑ የሚታወስ ቢሆንም በተለይ የወንዶቹ ፕሪምየር ሊግ ይጀመራል ተብሎ ከተነገረው ጥቅምት 4 ቀን ተገፍቶ ሊደረግ እንደሚችልም እየተሰማ ይገኛል።", "passage_id": "53dc606b97d92da0dc19025d8dfcd6cd" }, { "passage": "የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የ2012 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አንደኛ እና ሁለተኛ ዲቪዝዮን ውድድሮች የሚጀመርባቸውን ቀናት ይፋ አድርጓል።በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ሴቶች እግርኳስ ልማትና ውድድር ኮሚቴ ሰብሳቢ ሶፊያ አልማሙን ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማካሄድ ሁለቱ ሊጎች የሚጀመሩበት ቀን ይፋ አድርገዋል። በዚህም መሠረት አስራ ሁለት ክለቦችን እንደሚያሳትፍ የሚጠበቀው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አንደኛ ዲቪዚዮን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ስርዓት ኅዳር 13 የሚከናወን ሲሆን ኅዳር 27 ደግሞ ውድድሩ ይጀምራል ተብሏል፡፡ ዘጠኝ ክለቦችን ያሳትፋል የተባለው የሁለተኛ ዲቪዚዮን ውድድሩ ደግሞ የዕጣ ማውጣቱ ቀን ኅዳር 13 የሆነ ሲሆን ታህሳስ 18 ደግሞ ውድድሩ እንደሚጀመር ተገልጿል፡፡በተለያዘ በአንደኛ ዱቪዚዮን የሚወዳደረው ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ ከበጀት እና ከቡድኔ አቅም ጋር በአንደኛ ዲቪዚዮን መወዳደር አልችልም በሁለተኛ ዲቪዚዮን እንድወዳደር ይፈቀድልኝ ሲል ለፌዴሬሽኑ ደብዳቤን አስገብቷል፡፡ከአንደኛ ዲቪዝዮን የተውጣጡ ተጫዋቾችን ያካተተው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በአሁኑ ወቅት በታንዛኒያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡", "passage_id": "19d525154b26464d72e42a55119c5cb6" }, { "passage": "አስራ አንድ ክለቦችን የሚያሳትፈው የ2012 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ነገ በሚደረግ አንድ መርሐ ግብር ጅማሮውን ያደርጋል፡፡ነገ በብቸኝነት የሚደረገው ዲላ ላይ በ9:00 ጌዴኦ ዲላ ከ አርባምንጭ ከተማ የሚያደርጉት ጨዋታ ነው።የስድስት ወራት ደመወዝ ክፍያን ለቀድሞ አሰልጣኙ እየሩሳሌም ነጋሽ ባለመክፈሉ ምክንያት አዲስ ያስፈረማቸውን ተጫዋቾችን በፌድሬሽኑ ማፀደቅ ያልቻለው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመርሐ-ግብሩ መሠረት ድሬዳዋ ከተማን በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚገጥም የሚጠበቅ ቢሆንም ለአሰልጣኟ ክፍያን መፈፀም ካልቻለ በውድድሩ እንደማይሳተፍ ፌዴሬሽኑ ለክለቡ ማሳወቁን ሰምተናል፡፡መቐለ 70 እንደርታን አራፊ ቡድን የሚያደርገው ይህ ሳምንት በማድረግ ዕሁድ በ9:00 ሲቀጥል የዐምናው ቻምፒዮን አዳማ ከተማን ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ካጠናቀቀው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዳማ ላይ የሚያገናኘው ጨዋታ የዚህ ሳምንት ተጠባቂ ጨዋታ ነው።የጥሎ ማለፉ ቻምፒዮን ሀዋሳ ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም የፊታችን ማክሰኞ አቃቂ ቃሊቲን ይገጥማል፡፡ ረቡዕ ደግሞ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን የይራዘምልኝ ደብዳቤ አስገብቶ ተቀባይነት ያላገኘው እና ከመፍረስ ተርፎ በቅርቡ ዝግጅቱን የጀመረው አዲስ አበባ ከተማ መከላከያን ይገጥማል።የዘንድሮው ውድድር በ14 ክለቦች መካአል ለማካሄድ ታስቦ ነበረ ቢሆንም ዐምና በውድድሩ ላይ ሲሳተፍ የነበረው ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ በሁለተኛው ውድድር ለመሳተፍ በመወሰኑ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አዲስ አበባ ከፍተኛ ዲቪዝዮን በማምራቱ እንዲሁም ጥረት ኮርፖሬት በመፍረሱ በ11 ክለቦች መካከል የሚካሄድ ይሆናል።", "passage_id": "1c1fb2aab3866044ea6cb5bdafc0559b" }, { "passage": "ፌዴሬሽኑ ለተሳታፊዎቹ 32 ክለቦች በላከው ደብዳቤ መሰረት ከዛሬ መስከረም 5 ጀምሮ እስከ መስከረም 20 ቀን 2009 ድረስ የምዝገባ እና ፍቃድ ማውጫ ገደብ ያወጣ ሲሆን ለታዛቢዎች እና ዳኞች የሚከፈለውን አበል እስከ መስከረም 30 ድረስ እንዲያጠናቅቁ አሳስቧል፡፡ በቀነ ገደቡ ከፍለው የማይጨርሱ ክለቦችንም ከውድድር እንደሚሰርዝ ፌዴሬሽኑ አስታውቋል፡፡ የአምናው ውድድር በዳኞች እና ታዛቢዎች ክፍያ ለመጠናቀቅ ምክንያት የተጀመረበት ጊዜ መጓተቱ የሚታወስ ነው፡፡የከፍተኛ ሊግ ክለቦች ውድድሩ እስከሚጀመርበት ህዳር 3 ቀን 2009 ድረስ ተጫዋቾች የማዘዋወር መብት የሚኖራቸው ሲሆን ከመስከረም 9 ጀምሮ ተጫዋቾቻቸውን ማስመዝገብ እንደሚችሉ ታውቋል፡፡የ2009 የውድድር ዘን ከፍተኛ ሊግ በተባለበት ቀን የሚጀመር ከሆነ እስከ ሰኔ አጋማሽ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡ ይህም በ2008 ከነበረው ውድድር በተሸለ በጊዜ ተጠናቆ ወደ ፐሪሚየር ሊግ ለሚያልፉ ክለቦች ፋታ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የ2008 የውድድር ዘመን በነሃሴ ወር አጋማሽ መጠናቀቁ የሚታወስ ነው፡፡ የውድድር መጀመርያ ወቅቶች – ጥቅምት 20 ሲጀመር መስከረም 12 የውድድሩ ፕሮግራም ይወጣል – ህዳር 3 ሲጀመር ጥቅምት 3 የውድድሩ ፕሮግራም ይወጣል – የሚጀመርበት ቀን ያልተቆረጠ ሲሆን በቀጣዮቹ ቀናት ይታወቃል ተብሏል፡፡ ", "passage_id": "a0c9577f1db2b348deff039279c21245" } ]
7cd45f2624073fd4cd56e96ee02352f2
9f63d4d60f8d5c288db935de5a57e6bb
ከአገሩ በላይ ጃፓን ያከበረችው ኢትዮጵያዊ ጀግና
1928 ፋሺስት ጣሊያን በአምባገነኑ ቤኒቶ ሞሶሎኒ እየተመራ ኢትዮጵያን ወረረ። ምስጋና ለማይዘነጉት ጀግኖቹ አርበኞቻችን ይግባና ሞሶሎኒና ግብረአበሮቹ ብዙም ሳይደላደሉ ከአገር ቤት በቅሌት ተባረሩ። ከሃያ አራት ዓመታት በኋላ ታላቁ አበበ ቢቂላ የወራሪዎቹን መዲና ሮምን በባዶ እግሩ ወሮ ዓለምን ጉድ አሰኘ፤ የምን ጊዜም የማራቶን ንጉሱ የአፍሪካውያን ኩራትና የነፃነት ተምሳሌት እንዲሁም፤ የመጀመሪያው ጥቁር የማራቶን ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ በጥቁሮቹ በጀግኖቹ መታሰቢያ ወር የካቲት የጥቁር ህዝቦች ኩራት ሆኖ ከሃምሳ አምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመት ዋዜማ በሮም ኦሎምፒክ የፈፀመው ታሪካዊ ጀብድ በመላው ዓለም ያሉ ጥቁር አትሌቶችን በእጅጉ ያኮራና ያነሳሳ ነበር። ጷግሜ 5 ቀን 1952 አስራ ሰባተኛው የሮም ኦሎምፒያድ በታላቋ ሮም ጎዳናዎች አንድ ተዓምር ታየ፤ በርካቶች አይናቸውን ለማመን ተቸገሩ፤ በአንባገነኑ ሞሶሎኒ አገር በበርካታ ነጮች መሃል አንድ ጥቁር በባዶ እግሩ ታየ። የጥቁር ህዝቦች ተዓምርን ለመቀበል የሚተናነቃቸው ዘረኝነትን በደማቸው ያሰረፁ ነጮች እንዴት ይህ ሊሆን እንደቻለ ግራ ተጋቡ። አፍሪካውያንን ያኮራ ኢትዮጵያውያንን ከልብ ያስፈነጠዘ ታሪካዊ ድል። የአራት ዓመት ታዳጊ ሆኖ እናት አገሩ ኢትዮጵያ በጣሊያን ፋሺስት ስትወረር መጥፎውን ጊዜ ገና ባልጎለበተ የህፃን አዕምሮው የሚያስታውሰው አበበ ቢቂላ ሃያ ስድስት ዓመታት ጠብቆ ታላቁን የሮም ጎዳና በባዶ እግሩ ወሮ የማይደገመውን ታሪክ ሰራ። ከአራት ዓመት በኋላም 1956 በድጋሜ ጫማ አጥልቆ በቶኪዮ ኦሎምፒክ ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፎ ጥቁሮች በማይደፈረው ርቀት አሁን ላይ ቁንጮ እንዲሆኑ መሰረቱን አኖረ። እሱ በከፈተው በርም ቁጥር ስፍር የሌላቸው የማራቶን አትሌቶች ለዘመናት ርቀቱን የግላቸው አድርገው አሁን ድረስ ዘልቀዋል። የሻምበል አበበ ቢቂላ የህይወት ጉዞን የተመለከተ «ቤር ፉት ረነር» የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ያበቁት እንግሊዛዊው ፓል ራምባኒ«ድንቅ ድል ነበር። በጥቁር አፍሪካዊ የተገኘ የመጀመሪያው የወርቅ ድል! በእርግጥ በዚያን ወቅት ሌሎች ጥቁር አፍሪካውያን ሯጮችም ነበሩ። ግን የሚሮጡት ቅኝ ለገዟቸው የአውሮፓ ሀገራት ነበር። የአበበ ድል ታላቅ የሆነው ለዚያም ጭምር ነው። አዎን! አበበ ለዓለም አዲስ ነገር አሳየ። የአፍሪካ ህዝብ በእኩል መወዳደርና ማሸነፍ እንደሚችል አረጋገጠ›› ሲሉ የአበበ ድል ከስፖርትም የተሻገረ መሆኑን መስክረዋል። በታሪክ ላይ ሌላ የታሪክ ካባ ጥቅምት 11 ቀን 1957 ዓ.ም. ነበር። በጃፓን ዋና ከተማ በተሰናዳው ቶኪዮ ኦሎምፒክ ሮም ላይ በባዶ እግሩ በመሮጥ የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቀው አበበ ተገኝቷል። አበበ ከአራት ዓመት በፊት የአሸናፊነት ግምት ሳይሰጠው ባለድል ቢሆንም፤ በቶኪዮ ዳግም ታሪክ ስለመስራቱ ብዙዎች ጥርጣሬ አድሮባቸዋል።«ማሸነፍ ቀርቶ ውድድሩን መጨረሱ ትንግርት ነው»ሲሉ መላምት የሰጡም አልታጡም። የሮሙ ጀግና አበበ የትርፍ አንጀት ቀዶ ሕክምና ማድረጉና ሳያገግምም ከውድድር ሥፍራ መድረሱ ነበር ለዚህ ድምዳሜ እንዲበቁ ያደረጋቸው። በውድድሩ ተሳታፊ የሆኑት 15 አትሌቶች የኦሎምፒኩን የወርቅ ሜዳሊያ ለማግኘት እንዲቋምጡ አድርጓቸዋል። የሮሙን የባዶ እግር ታሪክ ቀይሮ ካልሲ አጥልቆ፣ ጫማውን ተጫምቶ በመጣው አበበ ፊት ላይ የሚነበብ የነበረው ገጽታ አስገራሚ ነበር። ከኦሎምፒኩ መዳረሻ 6 ሳምንታት ሲቀሩት የቀዶ ህክምና ማድረጉን ረስቶ ለሌላ ድል ራሱን ሲያሰናዳ ነበር የሚታየው። በዚህ መልኩ ውድድሩ የጀመረው አበበ እስከ መጀመሪያዎቹ 10 ኪሎ ሜትር የአውስትራሊያው ሮን ክለርክ ቢፎካከረውም ጥሎት በመሔድ ያለአንዳች ተቀናቃኝ በ2 ሰዓት 12 ደቂቃ 11.2 ሰኮንድ በድል አድራጊነት ፈጸመ። ከእርሱ በፊት ማንም ያልፈጸመውን፣ ከርሱም በኋላ ማንም ያላደረገውን የኦሎምፒክ ማራቶን ሁለት ጊዜ አከታትሎ የመውሰድ ታሪክ ሰራ። በጃፓናውያን ልብ ያበበው አበበበቶኪዮ ኦሎምፒክ የሜዳሊያ ሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ አንድ ትልቅ ክስተት ተፈጠረ። ክስተቱ ለኢትዮጵያውያን የሚያስቆጭ ቢመስልም ፤ በጃፓናዊያን ልብ ውስጥ አበበ ቢቂላ እድሜ ልክ እንዲታተም ያደረገ ነበር። የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር የጃፓን ባለሥልጣኖችም ሆኑ የሙዚቃ ባንዱ አያውቁትም ነበር። የመድረኩ አዘጋጆች ጃፓናውያን አንድ ነገር ዘየዱ። የማርሽ ባንዱ አጋጣሚውን ተጠቀመ። የጃፓንን ሕዝብ መዝሙር ለኢትዮጵያ ድል ማብሰሪያ አደረገው። ሕዝቡም ፈነደቀ። 17 ቁጥር መለያን ያጠለቀው አበበም በጃፓን ሕዝብ ልቦና ውስጥ ታተመ። ጃፓናውያን ለአበበ ክብር በቀዬያቸው ሐውልት አቁመውለታል። ጃፓናውያን ለአበበ ቢቂላ ያላቸው ጥልቅ ከበሬታን በ2006 ዓ.ም ኢትዮጵያ የመጡት የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ በ1957 ዓ.ም. በተካሄደው የቶኪዮ ኦሎምፒክ በማራቶን ድል ያደረገውን አበበ ቢቂላ ለማክበር ከልጁ ከየትናየት አበበ ቢቂላ ጋር በሸራተን በመገኘት ይሄንኑ ነበር ያረጋገጡት። ጠቅላይ ሚኒስትር አቤ የቶኪዮውን ሩጫ በልጅነታቸው እንደተመለከቱትና የአበበ ቢቂላ ተወዳዳሪዎቹን በርቀት ጥሎ ማሸነፉ ትንግርት መሆኑንም መስክረዋል።በኢትዮጵያ ስፖርት ትልቅ ስፍራ ያላቸው ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ በአንድ ወቅት በጃፓናውያን ዘንድ ትልቅ ቦታ ስላለው አበበ ቢቂላ የተናገሩትን እንጥቀስ። ‹‹…አበበ በድጋሚ በማሸነፉ በጃፓን ሕዝብ ለዘለዓለም የማይረሳ ትዝታ ትቷል። ዛሬም በጃፓን እንደጣዖት ይመለከቱታል። ማራቶን በጃፓን ውስጥ እንዲህ ተወዳጅ ሊሆን የቻለው ከአበበ ቢቂላ ድል በኋላ ነው። አሁንም ይኸው መንፈስ ቀጥሏል።››ብለው ነበር። በቶኪዮ ኦሎምፒክ በአጋጣሚ የተፈጠረችውን ታሪካዊ ክስተትን ዛሬ ያልረሱት ጃፓናውያን ከሁለት ሳምንት በፊት ጀግናውን ዘክረውታል። ጃፓናውያን የፍቅራቸው ገጸበረከት ሳይቀንስ ለሻምበል አበበ ቢቂላ መታሰቢያ ውድድር በጃፓን ካሳባ አድርገውለታል። በዚህ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታ ሃገራችንን የወከሉት አብዮት አብነትና እታለማሁ ስንታየሁ ሲያሸንፉ ውድድሩን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ እና የፌዴሬሽኑ የጽፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ እንዲሁም የሻምበል አበበ ቢቂላ ልጅ የትናየት አበበ ከስፍራው ተገኝተው ታድመዋል። በመድረኩ እንደተገለጸውም አበበ ቢቂላን የመዘከር ተግባሩ ከትውልድ የሚሻገር መሆኑን ጃፓናውያኑ አረጋግጠዋል።ነብይ በሀገሩ ይከበርበኢትዮጵያውያን ዘንድ አንዲት የምትታወቅ አባባል አለች «ነብይ በሀገሩ አይከበርም»።ሀገራችን በተለያዩ ጊዜያት የተፈጠሩና በተሰማሩበት መስክ ሀገራቸውን ለዓለም ያስተዋወቁ ዓለም አቀፍ ጀግኖች ባለቤት መሆኗ እሙን ነው። ለአብነት ከሚጠቀሱት መካከል ደግሞ አበበ ቢቂላ ቀዳሚ ነው። ጀግናው አበበ ቢቂላ በተለይ ከሮም እስከ ቶኪዮ በሰራቸው አንፀባራቂ ታሪኮች ኢትዮጵያን በዓለም ህዝብ ዘንድ አስተዋውቋል። አበበ እስከ ህልፈት ህይወቱ ድረስ ሀገሩን ሲያገለግል የኖረ የትውልድ አርዓያ የሆነ ጀግና ነው። የአበበ የታሪክ ተወዳሽነት በኢትዮጵያም ብቻ ሳይሆን በዓለም ሀገራት ሳይቀር ክብርና አድናቆት የተቸረው መሆኑ ክብሩን የበለጠ ያጎላዋል። የአበበ ቢቂላን ጀግንነት በማድነቅና በማክበርም በተለየ መልኩ ጃፓናውያን ይዘክሩታል። እንደ ጃፓናውያኑ ሁሉ ጣሊያንም ለአበበ ክብሩን አልነፈገችም። የሮም ኦሎምፒክ 50ኛ ዓመትን ስትዘክር አንድ ድልድይ በስሙ ሰይማለች። ሰሜን አፍሪካዊቷ አገር ሞሮኮም በስሙ ስቴድየም አኑራለታለች። በአሜሪካን አገር በየዓመቱ የሚካሄድ ዓለም አቀፍ ሽልማትም አበበን ለማስታወስ በስሙ ተሰይሞ ይገኛል።‹‹የአፍሪካ ማራቶን አባት›› ተብሎም በዶክመንተሪው ፊልም ላይ ታሪኩ ሰፍሯል። ታላቁን ሽልማትም ልጁ የትናየት አበበ ቢቂላ ተረክቧል። በኢትዮጵያ አበበ ቢቂላን በቋሚነት የሚዘክሩ አዲስ አበባና አዳማ ከተማ የሚገኙ ስታዲየሞች በስሙ ይጠራሉ። በቅርቡ በተመረቀው አንድነት ፓርክ ውስጥ ከቆመው መታሰቢያ በቀር ለአበበ በእናት ሀገሩ የቆመለት ታሪኩን የሚመጥን መታሰቢያ ሃውልት አይገኝም። ዓለም በተለይም ጃፓናውያን ያከበሩትን ያህል ግን ኢትዮጵያ አበበን አላከበረችውም። ወይም ስሙንና ታሪኩን የሚመጥን በብዛትም በጥራትም መታሰቢያ አላበጀችለትም። አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 19/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=24870
[ { "passage": " እርሱ ያንን መቼም አይረሳውም። ከኦሎምፒኩ ድሉ ማግስት የተዜመለትን። “ቀነኒሳ አንበሳ”። ይሄን ዜማ ሲሰማ በውስጡ ልዩ ሀሴት ይሰፍናል። ለውለታው የተዜመ ልዩ ስጦታው አድርጎ ይቆጥረዋል። አንዳች ልዩ ስሜትና ትዝታ ውስጥ የሚከተው ዜማ እንኳን ለተወዳደሪዎቹ ተመልካቹን በስሜት የናጠ ነው። “እልል በል ያገሬ ጎበዝ ለእምዬ ውለታ ወርቅ አመጣሁላት ልጇ ለክብሯ ስጦታ..” በረጅም ርቀት ውድድር የመጨረሻ ዙርን እንደ አጭር ርቀት የሚደመድም፤ በታላለቅ የውድድር መድረኮች በከፍታ የነገሰ ፤ እንደ አቦ ሸማኔ በፈጠኑ ጠንካራና ቀጫጭን እግሮቹ ተዓምር የሰራ ፤ የአገሩን ሰንደቅ አላማ በዓለም አደባባይ በክብር ከፍ አድርጎ ያወለበለበ፤ ህዝብ በእርሱ ድል እንዲፈነድቅ፣ ከያኒው ስለሱ አብዝቶ እንዲቀኝ ምክንያት የሆነ ኮከብ አትሌት ነው ቀነኒሳ በቀለ። ትጋት ጥንካሬና ፍጥነቱ “አንበሳው” የሚል ቅጥያ ያንሰዋል። ሀገር የሰጠውን ታላቅ አደራ አተልቆ የከፈለ ጀግና ነውና ። የዕረፍት ሰዓት ቆይታ ህይወትን ቀለል አድርጎ መኖር፤ የተካበዱ ጉዳዮችን ሳሳ አድርጎ ማየት የአትሌት ቀነኒሳ የኑሮ ፍልስፍናና ልምድ ነው። አዳዲስ ሞዴል ዘመናዊ አውቶሞቢሎችን የራሱ የማድረግ አቅም አለው፤ ነገር ግን ይህን ማድረግ አይወድም። የመረጠው ቦታ ላይ ቅንጡ ኑሮን መምራት ይችላል፤ ያን መሆን ግን አይፈልግም። ቀለል ያለ ህይወት ምቾት እንደሚፈጥርለት ይናገራል። የሚፈልገው በአኗኗሩ በዙሪያው ካሉ ሰዎች የተለየ አለመሆንን ነው። ያሻውን ከማድረግ ውጪ ለይሉኝታ ግድ የማይሰጠው ሰው መሆኑን ይናገራል። ለእርሱ ይህን ከማድረግ ነፍሱ በሀሴት የሚያጥለቀልቃት ከከተማ ርቀው ዓለም በቃኝ ብለው የመነኑ፤ የዓለምን ግሳንግስ ጠልተው የኮበለሉ፤ የምድርን ደስታ ንቀው ለነፍስ ያደሩ ባህታዊያንን አግኝቶ ከእርነሱ ጋር የእረፍት ጊዜውን ማሳለፍን ይመርጣል። ገዳማትና ራቅ ያሉ ተፈጥሯዊ ቦታዎች መገኘት እጅጉን ያስደስተዋል። ተፈጥሮ በራሱ የኳለውን አካባቢያዊ መልካም ምድር መመልከት ከምንም በላይ ያደንቃል። በእንዲህ ያለው ስፍራ መገኘትንም ሀሴት ያደርጋል። የዕረፍት ጊዜን ከቤተሰብ ጋር አብዛኛው የእረፍት ጊዜ ከቤተሰቡ ጋር ማሳለፍን የሚመርጠው አትሌት ቀነኒሳ ቤት ውስጥ ልዩ ቤተሰባዊ ድባብ በመፍጠር ከልጆቹ ጋር መጫወት፣ አዲስ የወጡ ፊልሞችን በጋራ መመልከት፣የተለያዩ የመናፈሻ ቦታዎች ላይ ቆይታን ማድረግ በእረፍት ቀኑ ያዘወትራል። ባለቤቱና ሶስቱ የአብራኩ ክፋይ ልጆቹ ‹‹ የደስታዬ ምንጭ ናቸው›› በማለት ለእነሱ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ይገልፃል። ከቃላትም በላይ ገጽታው ይመሰክራል። በማህበራዊ ህይወት በኩል ንቁ ተሳታፊ ነው አትሌት ቀነኒሳ። ለቅሶ፣ ሰርግና ልዩ ልዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አቅሙ በፈቀደው ሁሉ ይሳተፋል። በተጣበበ ጊዜውም ቢሆን ከጓደኞቹ ጋር የዕረፍት ሰዓት ቆይታ ያደርጋል። እዛ ደግሞ ቋንቋ ሁሉ ይቀየራል። አንድ አይነት ክንፍ ያላቸው አብረው ይበራሉም አይደል አባባሉ። የልብስ ምርጫ ለሚለብሰው ልብስ ምርጫ ግድ የሌለው ቀነኒሳ በተለይ በእርፍት ሰዓቱ ቀለል ያለ አለባባስን ያዘወትራል። በልብስ ፋሽን የመከተል ልምዱ አይደ ለም። ብቻ ከመልበሻ ሳጥኑ ውስጥ ያገኘውን ደስ የሚለውና ሲለብስ ይቀለኛል ብሎ የሚያስበውን ይመር ጣል። የባህል ምግብ በባለሙያ ክሽን ተደ ርጎ የተሰራ ዶሮ ወጥና ጨጨብሳ ከኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦች እጅጉን የሚወዳቸው ናቸው። ከገ በታው ላይ አትክልትና ፍራፍሬዎች አዘውትሮ ቢያገኝ ይመርጣል። ለሚያ ደርገው የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ለጤናው ጠቃሚ የተባለ የአመጋገብ ልምድ ይከተላል። ከራሱ አልፎ የቤተሰቡን ጤናማ የሆነ አመጋገብ ክትትል ያደርጋል። የአትሌቱ መልዕክት “ተፈጥሮ ሳያጓድል ሁሉን ነገር የቸራት ኢትዮ ጵያ ለሁላችን በቂ ናት። አንድነታችን አጠንክረን ልዩነታችንን አስወግደን ለሁላችን ምቹ የሆነች ሀገር ለመፍጠር በቅን ልቦና እንትጋ።” ከአትሌቱ ጋር የነበረን አጭር መሳጭና አስተማሪ ቆይታችንን የማበ ቃው አትሌቱ ከሚወ ደው ሙዚቃ “..ይቺ ባንዲራ አንበሳ ናት እድለኛ ዛሬም አኮራት አንበሳ ቀነኒ ኬኛ አንበሳዬ አንበሳ”… የሚለውን ስንኝ በመው ሰድ ነው። ሰላም!አዲስ ዘመን ግንቦት 2/2012ተገኝ ብሩ", "passage_id": "204e529026bf08f31cfce08130dc75b7" }, { "passage": "ትንናት ቅኔ፣ ዛሬ ደምና ወኔ የሆነን ዓባይ በጉባ ሰማይ ሥር በሀገሩ መሬት አርፎ እንዲሄድ ሲታቀድ የውሃውን ማደሪያና መሰንበቻ ቤት የሚሠራ አንድ ጠቢብ ሰው አስፈልጎ ነበር፡፡ ዓባይ በሀገሩ ሊያድር ቤት የሚሰራለትም የሀገሩ ልጅ ብቻ ነበር፡፡ የሚሰራው ሥራ መልዕክቱ አንድ ብቻ አልነበረም፡፡ የሀገርንና የሕዝብን አደራ መሸከም ግድ ይል ነበር፡፡ አደራው እንዲሁ በቀላሉ የሚታይም አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊያን እናቶች ከመቀነታቸው እየፈቱ ከጉያቸው ሥር እያወጡ በሰበሰቧት ሳንቲም ውስጥ ተስፋ፣ እመነት፣ ፍቅርና አንድነትም አብረው ሰጥተዋልና፡፡ያን አደራ የሚቀበለው ሰውም በምድጃ አጠገብ ተቀምጠው ጭስ አቅላቸውን እያሳታቸው ቃል ያስገቡትን እዳ ነበርና ነገሩ ያስፈራል፤ ያስደነግጣልም፡፡ በሌላ ደግሞ ሚሊዮን እናቶችን ከጨለማ አውጥቶ በኢትዮጵያውያን የተጣለበትን የእምነት እዳ ተወጥቶ በሕዝብ አደባባይ ሲደሰት ማዬትም ሌላ ተስፋ ነበር፡፡ ለዘመናት ታልሞ ሳይሳካ የቆየውን የዓባይ ማደሪያ በበላይነት መሥራት ከሚሊዮን ኢትዮጵያውያን መካከል ለአንድ እድለኛ መሰጠት ያስፈልግ ነበርና ከሚሊዮኖች የተመረጠው በኃላፊነት ተረከበው፡፡ ለዚህ የተመረጡትም ኢንጂነር ስመኛው በቀለ ነበሩ፡፡ዓባይ በሀገሩ ምድር እንዲሰነብት ኢትዮጵያውያን ተስማሙ፡፡ በወረሃ መጋቢት የማረፊያ ቤቱ ሊሰራለት የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ፡፡ ኢትዮጵያውያን ጮቤ ረገጡ፡፡ ሁሉም ዓባይ ላይ ዘመተ፤ ሥራውም ተጀመረ፡፡ ከሚሊዮኖች የተመረጡት የግድቡ ሥራ አስኪያጅም በጭስ ተደብቀው አደራ ያሏቸውን ኢትዮጵያዊያንን ድምጽ በእዝነ ልቦናቸው እያዳመጡ ከቤተሰብ ተለይተው ወደዚያ በረሃ ወረዱ፡፡ታላቁ ሰው ከቤተሰብ ርቀው፣ እንደ ሌሎች አባቶች ከልጆቻቸው ጋር ሳይጫወቱ፣ ቀዝቀዝ ባለ አየር ሳይናፍሱ አደራቸውን ለመወጣት ኳተኑ። በኢትዮጵያውያን ታምኖ ጎድሎ መገኜት ከባድ ነበርና የራሳቸውን ደስታ ወደ ጎን ትተው የአገርን ደስታ ለማስቀደም ደከሙ፡፡ ከሙያ አጋሮቻቸውና ከኢትዮጵያውያን ጋር ሆነው ከመሠረት አንስተው ሥራውን ከፍ አደረጉ፡፡ዳሩ ግን የጀመሩትን መቋጨት አልቻሉም፡፡ ሥራውን ጨርሰው ይሞገሱበታል በተባለው አደባባይ ላይ ሕይወታቸው አልፎ ተገኙና ኢትዮጵያዊያን ደነገጡ፡፡ ሀዘኑም ከፍ አለ፡፡ ከሁሉም ግን ከጉባ በረሃ ተመልሰው ፍቅር እስኪሰጧቸው ሲጠባበቁ ለነበሩ ቤተሰቦቻቸው ሐዘኑ ከባድ ነበር፡፡ በሀሩር ሥር የተደበቀን መብራት ፈንጥቀው በጨለማ ውስጥ የኖረውን የኢትዮጵያዊ ለማስደሰት የጀመሩት ውጥን መስቀል አደባባይ ላይ ተቋጨ፡፡ ለኢትዮጵያውያንም የተጀመረ ሥራ፣ የጎመራ ፍቅር፣ የተባ አንድነት፣ ከፍ ያለ መተሳሰብ ትተው እንዲጨርሱት በመንፈስ አበርትተው በአንደበታቸው ሳይሰናበቱ ላይመለሱ አሸለቡ፡፡የኢትዮጵያውያን ተስፋ በስሎ ሳያዩት፣ አብርቶ ሳይመለከቱት በጎን የሀገር ፍቅር፣ በጎን ደግሞ የቤተሰብ ፍቅር እንዳቃጠላቸው፤ በላይ የጉባ በረሃ እንደገረፋቸው ወደማይቀርበት ተሰናበቱ፡፡\nኢንጂነር ስመኘው ለዘመናት የተመኘነውንና የተመኙትን ፈፅመው ባያሳዩንም የማይደፈር ደፍረው፣ ያልተጀመረ አስጀምረው አጋምሰው ጥለውት ስለሄዱ የተጀመረው አልቆመም፤ ሥራው ቀጠለ፡፡ የዓባይ ግድብ ገና ሲታለም አንስቶ ከፍ ያለ ግምት ቢሰጠውም በተለይም ግን በቅርብ ዓመታት የዓለም አቀፍ አጀንዳ፣ የአንድነት፣ የጽናት እና የጀግንነት መለኪያ፣ የዜግነት መፈተኛ ሆኗል፡፡ ግብፅ አትንኩብኝ፣ ኢትዮጵያም በጋራ እንጠቀም ስትል የባለቤቱና የጎረቤቱ ውይይትና ድርድር ቀልብ ሳበ፡፡የሽያጭ ፍንጥር ለመጠጣት የቋመጡ የሚመስሉ ጥቂቶችም የዓባይን መሸጥ በአደባባይ “ሲያበስሩ” ሰነበቱ፡፡ ሥራው እየቀጠለ፣ ድርድሩም እየተካሄደ ባለበት ጊዜ የዓባይ ውሃ ከጉዞው ማረፍ ጀመረ፡፡ በጉባ መሬት ላይ ተኝቶ እንደ ወዳጁ ጣና ፈልሰስ ብሎ ተኛ፡፡ቢዘያ ስፍራ ውሃ ብቻ ሳይሆን የተሞላው፣ ታሪክ፣ ክብር፣ ሉዓላዊነትና አንድነትም ጭምር ነውና በውጥረት መካከል የዓባይ ውሃ የመጀመሪያ ሙሌት መጠናቀቀቅ ሲሰማ ኢትዮጵያዊነትን ለሚወዱ ኢትዮጵያዊያን ደስታው እጥፍ ድርብ ሆነ፡፡ የሽያጭ ፍንጥር ለመጠጣት ሲቋምጡ የነበሩትም አፈሩ፡፡ ማንነው ወንዱ ሲሉት የነበሩትም ደነገጡ፡፡", "passage_id": "8a9d242fb4d9b39a754304c414d1c56e" }, { "passage": " ከዓለም እስከ አህጉር፣ ከአህጉር እስከ አገር፣ ከአገር እስከ መንደር ከዚያም ማህበረሰብ እስከ ግለሰብ፣ በስፖርት ልቡ ያልተሳበና በፍቅሩ ያልተንበረከከ የለም።ስፖርት ሰላም ፣ፍቅር ፣የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም።ሁለት የተለያዩ አገራት ያወዳጃል። በአገር ፍቅር ስሜት ያስተሳስራል።ያፋቅራል።በእርግጥ አንዳንዶች ውጤትን ከስፖርታዊ ጨዋነት አስበልጠው የግል ጥቅማቸውን ሲያስቀድሙ ይስተዋላል። ከዚህ በአንፃሩ የግል ፍላጎታቸውን ችላ በማለት በስፖርታዊ ስነ ምግባር የታነፁ መኖራቸው የማይካድ ሃቅ ነው።በአትሌቲክሱ የውድድር ፍልሚያ ኬንያውያን በተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ውድድሮች ላይ በርካታ ወገኖችን አስደንቀዋል።አስጭብጭበዋል።በውድድር አሸናፊ ሆነው የታዩትን ያህልም ከአንዴም ሁለት ጊዜ በስፖርታዊ ጨዋነትና ሰብዓዊነት ተግባር የታነፁ ስለመሆናቸውም አስመስክረው የሚሊየኖችን ልብ ሲያሸንፉ ታይተዋል።።የምስራቅ አፍሪካዊቷ አገር አትሌት ከሰሞኑም ይህን በስፖርታዊ ጨዋነት መርህ የታነፀ ሰብዓዊነት ተግባር ደግሞ አሳይቷል።ትዕይንቱ የተከሰተው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማህበር የነሃስ ሜዳሊያ በሚሰጠውና ከቀናት በፊት በተካሄደው የናይይጄሪያ ዓለም አቀፍ የ10 ኪሎ\nሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ነው።የታሪኩ ባለቤት ሲሞን ቺፕሮት ይባላል።ኬንያዊ የረጅም ሩጫ አትሌት ነው።በዚህ የ10 ኪሎ\nሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ሲሳተፍ አራተኛው ሲሆን፣ ከሶስት ዓመት በፊት ደግሞ ባለድል መሆን ችሏል።ባሳለፍነው አመት ደግሞ ሁለተኛ ሆኖ ጨርሷል።ክስተቱ እንዲህ ነው። ሲሞን ቼፐሮት የዘንድሮውን ውድድር እየመራ ለመጨረስ የተወሰኑ ሜትሮች ብቻ ቀርተውታል።ውድድሩን ለሁለተኛ ጊዜ በማሸነፍ የመጀመሪያው የሚሆንበትን ታሪክ ለመፃፍ ማንም ሊያቆመው አይቻለውም።ይሁንና በዚህ ቅፅበት ሌላኛው የአገሩ ልጅና ብርቱ ተቀናቃኙ የሆነው ኬኔት ኪፕኬሞይ ድንገት ሲዝለፈለፍ ይመለከታል።ክስተቱን ያስተዋለው ሲሞን ቼፕሮት ግን የአገሩን ልጅ ጥሎት ለመግባት አልወሰነም።ውድድሩን አሸንፎ አንደኛ የመባል ስሜቱን አላዳመጠም።ውድድሩን ለሁለተኛ ጊዜ በማሸነፍ የመጀመሪያው የሚሆንበት ታሪክ ለመጻፍ አልቸኮለም።አትሌቱ የተፎካካሪውን ውድቀት እንደ መልካም አጋጣሚ ከመጠቀም ይልቅ ብዙዎቹን ባስገረመ መልኩ ሩጫውን በማቋረጥ ጓደኛውን ከወደቀበት ደግፎ አንስቶ ልባዊ ወንድምነቱን በማሳየት በርካታ ወገኖችን አስደምሟል። ሁለቱ አትሌቶችም ቀስ ብለው በመሮጥ ውድድሩን 15ኛ እና\n16ኛ ሆነው የፈፀሙ ሲሆን አንደኛ መውጣት የሚችለው ሲሞንም ተሸንፏል።አትሌቱ ከፊቱ የሚጠብቀውን የወርቅ ሜዳሊያና የአሸናፊነቱን ሽልማት ገንዘቡን በመተውና ይህ ሁሉ ከሰው እንደሚያንስ በማሳብ የፈፀመው መልካም ተግባር በሚሊየን የሚቆጠሩ ልቦችን ማሸናፍ ችሏል።የወርቅ ሜዳሊያውን ትቶ ከወርቅ በላይ የሆነ ጀብዱ በመፈፀም፤ ከወርቅ ሜዳሊያው ይልቅ ሰብአዊነት እንደሚልቅ ለመላው ለዓለም   አሳይቷል።ሜዳሊያ ሳይሆን ልብ ያሸነፈውና በውድድሩ ስፍራ ሆነው ውድድሩን የተመለከቱትን በሺዎች የሚቆጠሩ ብቻም ሳይሆን በአህጉር ዓቀፍ ደረጃ በቴሌቪዥን መስኮት የሚመለከቱትን ያስደነቀ አትሌት ፤ማሸነፍ ማለት ሁሌ አንደኛ መውጣት ማለት አይደለም፤ሁሌ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኛት አይደለም። አንዳንዴ ተሸንፈህ አሸናፊ ትሆናለህ፣ መጨረሻ ወጥተህ ክብርን ጀግንነትን ትጎናፀፋለህ አሰኝቷል።‹‹በአንድ ወቅት አባቴ፤ በመንገድህ ላይ የታመመ ሰው ስትመለከት አልፈኸው ጉዞህን አትቀጥል፤ ይልቅ እርዳው፤ ብሎኝ ነበር፤ የአገሬውን ልጅ ወድቆ ስመለከተው ይህ ወደ አእምሮዬ መጣ፤ እናም ለራሴ ሳላስብ ልረዳው ወሰንኩ ››ያለው አትሌቱ፤ መሰል ተግባሩም ለመጪው ትውልድ አርእያነት ያለው ስለመሆኑ ተናግሯል።የአትሌቱ ተግባርም የወርቅ ሜዳሊያ ከማግኘት ይልቅ ወርቃማ ልብ መያዝ ይበልጥ ያነግሳልና ይህም እውነተኛው የስፖርት ጽንሰ ሃሳብ መገለጫ ነው አሰኝቷል። በዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር የናይጄሪያ ተወካይ ማይክ ልቴሟግቦር አትሌቱን ‹፣ጀግናችን››ሲሉ አሞካሽተውታል፡፡ለፈፀመው የሰብዓዊነት አኩሪ ገድልም አንድ ሚሊየን ሽልንግ አበርክተውለታል።የቺፕሮትን ተግባር\nበማወደስ፤ ተረጂው አትሌት\nበበኩሉ፤ ‹‹ሁሉም አትሌት\nይህን መሰል ተግባር\nአይፈፅምም፤ሲሞን መልካም\nሰው ነው፤ በውድድሩ\nእኔን ለማርዳት ያሰው\nመልካምነትም እጅጉን አስድንቆኛል››\nሲል ተደምጧል። አሸንፎ\nሜዳሊያውን ከወሰደው ኢትዮጵያዊ\nበላይ ሲሞን ጀግና\nተብሎ ዘላለማዊ ስምና\nዝናን አትርፏል።አዲስ ዘመን ግንቦት 27/2011 ", "passage_id": "ea9ee4c32daedd909149824d13b5ab5d" }, { "passage": "ኢትዮጵያ ከፍተኛ ውጤት ባስመዘገበችበት የሲድኒ ኦሊምፒክ 5ሺ ሜትር ካሸነፈ በኋላ ደስታውን የገለፀበት የተለየ መንገድ በብዙዎች ዘንድ እስካሁንም እንዲታወስ ያደርገዋል፡፡ በወቅቱ ወጣት አትሌት የወርቅ ሜዳሊያ ማስመዝገቡ ከፍተኛ ደስታ የፈጠረ ቢሆንም በአትሌቲክስ ቤተሰቡ ዘንድ ተተኪ አትሌት መታየቱ ግን የተለየ ስሜት ያስገኘ ነበር፡፡ ነገር ግን ድንገት የታየው ተስፋ በቀጣይነቱ ሊገፋ አልቻለም፡፡ የያኔው ወጣት አትሌት ሚሊዮን ወልዴ ከሲድኒ ኦሊምፒክ ጣፋጭ ድሉ በኋላ በሌሎች ታላላቅ ውድድሮች ተጨማሪ ስኬት ያስመዘግባል ተብሎ እምነት ቢጣልበትም በውድድሮች ሳይታይ ቀርቷል፡፡ ውድድሩን እንዳጠናቀቀ ድሉን ያከበረበት መንገድ ከአብዛኛው ህዝብ የትዝታ ማህደር የማይደበዝዘውና እስካሁንም ለዓመታት መጥፋቱ የስፖርቱ ቤተሰብ ጥያቄ የሆነው የቀድሞው አትሌት ሚሊዮን ወልዴ ከጥቂት ዓመታት በፊት ለትምህርት ወደ አሜሪካን አገር እንደተጓዘ ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያ በጀግኖች አትሌቶቿ አራት የወርቅ፣ አንድ የብርና ሶስት የነሃስ በጥቅሉ በስምንት ሜዳሊያዎች ከምንጊዜውም የተሻለ ውጤት ባስመዘገበችበት የሲድኒ ኦሊምፒክ አንድ የወርቅ ሜዳሊያ እንዲመዘገብ ምክንያት የሆነው ሚሊዮን ለረጅም ጊዜ በትራክ እንዲሁም በተለያዩ ውድድሮች ባይታይም አሁን በባህር ማዶ ታዳጊዎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡ አትሌቱ በተለይ የታወቀው በሲድኒው ኦሊምፒክ ይሁን እንጂ በዓለም አቀፍ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው እአአ በ1998 ሲሆን፤ በተሳተፈበት ርቀት የዓለም ወጣቶች ቻምፒዮን ነበር፡፡ በቀጣዩ ዓመት ደግሞ በቤት ውስጥ ቻምፒዮና ሃገሩን በመወከል ከታላቁ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ጋር ተሳትፎ በ3ሺ ሜትር የነሃስ ተሸላሚ ሆኗል:: ራን ብሎግ ራን የተሰኘው ድረገጽ ከአትሌቱ ጋር በነበረው ቃለምልልስ አንጋፋው አትሌት በአሜሪካ በሚገኝ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የሃገር አቋራጭ አትሌት ተማሪዎችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡ ወደ አትሌቲክስ ስፖርት እንዴት እንደገባ የተጠየቀው ሚሊዮን ‹‹ልጅ እያለሁ ኳስ ነበር የምጫወተው፤ ለሌሎች ስፖርቶችም ፍላጎት ነበረኝ፡፡ እኔ ከጓደኞቼ ጋር ኳስ በምጫወትበት ሜዳ ላይም በርካታ አትሌቶች በየቀኑ ልምምድ ሲሰሩ እመለከት ነበር፤ ይህም ፍላጎት አሳድሮብኝ ወደ ስፖርቱ ልገባ ቻልኩ›› ሲል መነሻውን አስታውሷል፡፡ ፈጣን ሯጭነቱ ወደ አትሌትነት ለመሸጋገሩ ምክንያት ሲሆን፤ ወደ ክለብ ለመቀላቀልም የወሰደበት ጊዜ አጭር ነበር፡፡ የገባበት ክለብ በሃገሪቷ የተሻለ ከሚባሉት መካከል በመሆኑም በውድድር ተሳታፊ ለመሆን ረጅም ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ አሁን እያሰለጠነ በሚገኘው የሃገር አቋራጭ ውድድር ተሳታፊ የሆነው እአአ በ1996 የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ ታውን አስተናጋጅ የነበረችበት ውድድር ነው፡፡ በወቅቱ አሸናፊ በመሆኑ ከሃገሪቷ መሪ ኔልሰን ማንዴላ እጅ ሜዳሊያ የተበረከተለትን አጋጣሚም የማይዘነጋው ነው:: ሌላኛው የማይዘነጋና አስደሳቹ አጋጣሚ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያን ማጥለቅ ነው፡፡ ‹‹በህይወቴ ትልቅ ስፍራ ያለውም ነው፤ መንግስትን ጨምሮ ከበርካታ አካላትም ሽልማቶችን አግኝተናል›› በማለትም ሚሊዮን ያለፈውን ስኬት ያስታውሳል፡፡ በአሜሪካውያንና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መካከል ያሉትን ልዩነቶች እንዲጠቅስ የተጠየቀው ሚሊዮን የጎላ ልዩነት አለመኖሩን አንስቷል፡፡ ነገር ግን አሜሪካ በተሟላ የስልጠና ቁሳቁስና በሳይንሳዊ ስልጠና አትሌቶችን ስትደግፍ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ በተወሰነ መልኩ ለስልጠና አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁስን ብቻ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታ ላይ ልዩነት እንዳለ ያብራራል፡፡ ለወጣት አትሌቶች ስኬታማነት ልምዱን ያካፈለው አሰልጣኝ ሚሊዮን ወጣት አትሌቶች ለራሳቸው ግብ በማስቀመጥ ጠንክረው መስራትና ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ያስቀምጣል:: ይህንን የሚያደርጉ ከሆነም በብቃታቸው ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ያለውን እምነት ገልጿል፡፡ አዲስ ዘመን ጥር 6/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "b9b061b8a07fb2412bbd4d1b0da91348" }, { "passage": "አንዳንዶች በሕይወት ይመስ ሉታል፤ አባጣ ጎርባጣ በሚበዛው ውድድር። ሌሎች ደግሞ በአትሌቲክስ ስፖርት ከባድና አስቸጋሪ በማለት ይገልጹታል የሀገር አቋራጭ ውድድርን። ውድድሩ፤ ወጥነት በሌለው መስክ፤ በርካታ የሚተጣጠፉ መስመሮችን እየተከተሉ፣ በጭቃ፣ በአቧራ፣ በረግረጋማ፣ በትናንሽ ጉብታዎችና ኮረብታማ ስፍራዎች ላይ መሮጥንም ይጠይቃል። በዝናባማ፣ በበረ ዷማ፣ በከፍተኛ ሙቀትና ጉም በሸፈነው የአየር ሁኔታም ኪሎሜትሮችን ማቋረጥ በእርግጥም ከባድ ጽናትን ይጠይቃል። በመሆኑም የትኛውም አትሌት ሊሳተ ፍበት አይችልም። እጅግ ከባድ እና ፈታኝ ከሚባሉ እልህ አስጨራሽ የአትሌቲክስ ውድድሮች መካከል በቅድሚያ የሚጠ ቀሰው ሀገር አቋራጭ ጥንካሬን ይጠይቃል። የምሥራቅ አፍሪካዎቹ ጎረቤታሞች ኢትዮጵያ እና ኬንያ ግን በዚህ ውድድር የተካኑ አትሌቶች ባለቤቶች በመሆናቸው የውድድሩን ክብር በተደጋጋሚ የግላቸው አድርገዋል። 43 ዓመታትን በተሻገረው የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ታሪክ በርካታ ክስተ ቶችም ታይተዋል። ከእነዚህ ውድድሮች መካከልም እአአ በ2007 በሞምባሳ የተካሄደው ውድድር ይጠቀሳል። በዚህ\nውድድር ላይ የታየው ድራማዊ ትዕይንትም እስካሁን የሚታወስ ነው። ዓለምአቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበርም በመጪው ቅዳሜ በዴንማርክ የሚካሄደውን ውድድር አስመልክቶ በድረገጹ ላይ ሁኔታውን በተንቀሳቃሽ ምስል ደግፎ አስታውሷል። በዚህ ውድድር በመንገስ ቅድሚያውን የያዘው ኢትዮጵያዊው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ነው። አምስት የወርቅና አንድ የብር ሜዳሊያዎችን የግሉ በማድረግም ባለክብረወሰን ነው። እአአ በ2004 በብራሰልስ በተካሄደው ሻምፒዮና ኢትዮጵያዊውያኑ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለ፣ገብረእግዚአብሔር ገብረማርያም እና ስለሺ ስህን በሰከንዶች ልዩነት ተቀዳድመው ከአንድ እስከ ሦስት ያለውን ደረጃ የወሰዱበት ውድድር እስካሁንም እጅግ ስኬታማ ሆኖ ይጠቀሳል። ይህ አትሌት በሀገር አቋራጭ ውድድሮች መሳተፍ የጀመረው በወጣትነት ዕድሜው ሲሆን፤ በወጣቶች ዘርፍ በሚካሄደው አጭር ርቀትም ሆነ በአዋቂዎች ምድብ በሚካሄደው ረጅም ርቀት ተስተካካይ ያልተገኘለትን ስኬት አጣጥሟል። እአአ በ2001 በብር\nሜዳሊያ በተቀላቀለው የውድድር ዓውድ ላይም ከስድስት ዓመታት በላይ ተሳትፎ በአሸናፊነት አጠናቋል። በኬንያ ሞምባሳ በተካሄደው ውድድር ግን ንጉሱ ዳግም ድሉን ሊጨብጥ አልተቻለውም። ይህ የሆነው በርቀቱ እጅግ ስኬታማ በሆኑት ኬንያውያንም አልነበረም። ድራማዊ በሆነው ክስተት አሸናፊነቱን አሳልፎ ለጎረቤት ሀገር በመስ ጠቱና ርቀቱንም ለማጠናቀቅ ባለመቻሉ እንጂ። በጎልፍ ሜዳ ላይ በተዘጋጀው ውድድር፤ ቀነኒሳ እንደተለመደው በርቀቱ አመዛኙን ክፍል በመሪነት ሲሸፍን ነበር የቆየው። የሀገሩ ልጆች እና አሰልጣኞቹ ብቻም ሳይሆን ውድድሩን ለመከታተል በስፍራው የተገኙ ሁሉ የአሸናፊነት ግምት ወደ ርቀቱ ንጉስ አጋድሎም ነበር። ርቀቱን ከግማሽ በላይ ከተጓዘ በኃላ ግን የቀነኒሳ አሯሯጥ እንደ አጀማመሩ ፍጥነት የተሞላበት እንዳልሆነ ታየ። ይህንን አጋጣሚ የተጠቀመው ኤርትራዊው የጎዳና ላይ አትሌት ዘረሰናይ ታደሰም ኃይል በመጨመር በመካከላቸው ያለውን ርቀት ለማጥበብ ሙከራ ማድረጉን ተያያዘው። ሲያስከትለው የነበረው አትሌት እንደቀረበው የታወቀው ቀነኒሳም በድጋሚ ርቀቱን ለማስፋት የቻለውን ያህል ጥረት አድርጓል። ውድድሩን ለመመልከት ከቦታው የተገኙት ደጋፊዎችም የሁለቱ አትሌቶች ትንቅንቅ ስቧቸው አብረዋቸው በመሮጥም ጭምር ሞራል ሲሰጧቸው ቆዩ። ኤርትራዊው ዘረሰናይም ቀነኒሳን በመቅደም በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ለማስፋት ፍጥነቱን ጨመረ። የበላይነቱ የተያዘበት ቀነኒሳም ቀዳሚነቱን ለማስመለስ የነበረውን ኃይል መጠቀሙ አትሌቶቹ ከርቀቱ የመጨረሻ መስመር ላይ የደረሱ የሚመስል አኳኋን ነበረው። ጥረቱ የተሳካለት ቀነኒሳ በድጋሚ ቀዳሚነቱን አስመለሰ። በመካከላቸው ያለው ርቀት በድጋሚ መስፋትም የርቀቱ ክብር ከኢትዮጵያዊው አትሌት እንደማያልፍ ለማረጋገጥ የሚያስችል ነበር። ከ29ኛ\nደቂቃ በኋላም በድጋሚ መሪ የነበረው ቀነኒሳ ፍጥነቱ እየቀነሰ በመምጣቱ ልዩነታቸው ከመጥበብ አልፎ ዘረሰናይ ለመቅደም ቻለ። ይህንን ዕድል ዳግመኛ ማበላሸት ያልፈለገው ኤርትራዊው የግማሽ ማራቶን አትሌት ቀነኒሳን በቀደመበት ቅጽበት ወደኋላው እየተገላመጠ በከፍተኛ ኃይል ወደፊት መስፈንጠሩን ተያያዘው። በቀነኒሳ እና በአትሌቱ መካከል ያለው ርቀት ልዩነቱን ስላሰፋው ሊከተለው እንጂ ሊደርስበት አልቻለም ነበር። በቻለው ፍጥነት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ የነበረው ጥረትም በተመሳሳይ ሊሳካ ባለመ ቻሉ ስኬታማው አትሌት ውድድሩን ለማቋረጥ ተገደደ። ይህ ውድድር 800 ሜትር ሲቀረው ራሱን ከተወዳዳሪነት ውጪ ያደረገውን ኢትዮጵያ አትሌት ንግስናውን ለሌላኛው አትሌት ያስረከበበት ሆነ። ይሁን እንጂ በሞቃታማው የአየር ሁኔታ ያን ያህል ፉክክር ይደረጋል በሚል የጠበቀ ባይኖርም በመም ላይ የሚካሄድ ውድድር እስኪመስል ድረስ የሁለቱ አትሌቶች ፉክክር ከአትሌቲክስ ወዳጆች ልቦና የሚሰረዝ አይደለም። ታሪክም ውድድሩ ተወዳጅና ተናፋቂ እንዲሆን ያደረገውን አትሌት በወርቅ ቀለም ከትቧል፤ይህ ውድድር ሲመጣም ቀነኒሳና ገድሎቹ ይዘከራሉ።አዲስ ዘመን መጋቢት 19/2011በብርሃን ፋይሳ", "passage_id": "90c15bf73588eebc39e87cd1367fc65d" } ]
05a8426ed67fad215ffea83294d5934c
b916d0b934b0042fc5abfe1f8e9808ab
ለብሄራዊ ስታዲየም የሁለተኛ ዙር ግንባታ ዝግጅት እየተደረገ ነው
በአደይ አበባ ቅርፅ እየተገነባ የሚገኘው ዘመናዊው ብሄራዊ ስታዲየም ሁለተኛ ዙር ግንባታ በቅርቡ የሚጀመር መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አስታወቀ።መንግስት ለግንባታው ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ በመሆኑ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ጥረት እንደሚደረግም ተገልጿል። በታህሳስ ወር 2008 ዓ.ም የተጀመረው የብሄራዊ ስታዲየም ግንባታ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ ለመሸጋገር በዝግጅት ላይ ይገኛል።በአዲስ አበባ ከተማ በሁለት ዙር የሚገነባው ስታዲየሙ የመጀመሪያ ዙር ግንባታ 99 በመቶ መድረሱን ኮሚሽኑ ትናንት ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ባዘጋጀው የጉብኝት መርሃ ግብር ወቅት አስታውቋል።ቀሪው አንድ መቶኛ የሜዳ ግንባታና የመም ማንጠፍ ስራዎች፤ በመጀመሪያው ውል በስታዲየሙ ግንባታ ማጠቃለያ ላይ የሚገነቡ ይሆናል።የሁለተኛው ምዕራፍ ስራ የጨረታ ሂደት የተጠናቀቀ ሲሆን፤ ቴክኒካዊ ጉዳዮች በአማካሪው ድርጅት በመገምገም ላይ ይገኛል።በመሆኑም በቅርቡ ተጠናቆ የስምምነት ፊርማ ስነ ስርዓት ሲካሄድ የተቋራጩ ማንነት እንዲሁም የገንዘብ መጠን ለህዝብ ይፋ ይሆናል። ከፍተኛ ወጪ በሚጠይቀው በዚህ ፕሮጀክት መንግስት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ ሲሆን፤ አስፈላጊውን ሁሉ በማሟላት በተቀመጠው ጊዜ እንዲጠናቀቅ ጥረት እያደረገ መሆኑም ተገልጿል።የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ የተቀመጠለት የጊዜ ገደብ 900 ቀናት ቢሆንም ከውጪ በሚገቡ ቁሳቁስ ምክንያት ጥቂት መዘግየት አጋጥሟል።ይህ ግንባታም ከሁለት ዓመት ተኩል እስከ ሶስት ዓመት የሚፈጅ ሲሆን፤ በምንዛሬ ችግር በተለያዩ ክልሎች እንደሚስተዋለው መዘግየት እንዳያጋጥም መንግስት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ገልጸዋል። በጉብኝቱ ተገኝተው መግለጫ የሰጡት ኮሚሽነሩ፤ በመንግስት በኩል ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ልዩ ትኩረት መስጠቱን አረጋግጠዋል።የመጀመሪያው ዙር ግንባታ በአጠቃላይ 2 ነጥብ 47 ቢሊየን ብር ወጪ ተደርጓል።ለሁለተኛው ዙር ግንባታ ከዚህ በላይ የሚያስፈልግ ሲሆን፤ መንግስት ለዚህ ዓመት ብቻ 2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር መድቧል። ሁለተኛው ዙር ግንባታ በስታዲየሙ፤ የዙሪያ ጣራ ማልበስ፣ የደህንነትና የድምጽ ሲስተሞችን መዘርጋት፣ የወንበርና ስክሪኖች ገጠማ እንዲሁም የተለያዩ ክፍሎች፣ ቢሮዎችና የመገናኛ ብዙሃን መገልገያ ክፍሎች ስራን ያጠቃልላል። ከስታዲየሙ ውጪም፤ ቢሮዎች፣ የዕቃ ማከማቻ ክፍሎች፣ የመኪና ማቆሚያና ሄሊኮፕተር ማረፊያ ስፍራዎች፣ ቲያትር ቤት፣ የባድሜንተን እና ሶስት በአንድ መጫወቻ ሜዳዎች፣ ሁለት የመለማመጃ ሜዳዎችን እንዲሁም በስታዲየሙ አጠገብ የሚያልፈውን ወንዝ አልምቶ ለመዝናኛ ማዋልን የያዘ ሰፊ ስራ ነው። አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 22/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=25006
[ { "passage": "በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ግንባታቸው ያልተጠናቀቁ እና በግንባታ ላይ የሚገኙ የእግር ኳስ ሜዳዎችን የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ዛሬ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የመስክ ምልከታ እንደሚያደርጉ ታውቋል።የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ በሆኑት ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) የሚመራው ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ግንባታቸው ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ እና በግንባታ ላይ የሚገኙ የእግርኳስ ሜዳዎችን ዛሬ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጀምሮ ሲጎበኙ የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይለሰማዕት መርሀ ጥበብ እና የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኃይለኢየሱ ፍስሀ (ኢንጂነር) እንዲሁም ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት እንደሚገኙ ታውቋል።ቡድኑ በጉብኝቱ ከሚያካትታቸው የእግር ኳስ ሜዳዎች መካከል ያለፉትን ሁለት ዓመታት በግንባታ ምክንያት አገልግሎት መስጠት ያቆመው እና አሁን ግንባታው ወደ መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሶ ከየካቲት ወር መጨረሻ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀው የአበበ ቢቂላ ስታድየም አንዱ ሲሆን፤ ለረጅም ጊዜያት ግንባታው ያልተጠናቀቀው እና አሁን ወደ መጨረሻው ምዕራፍ ላይ የደረሰው የአቃቂ ስታድየምም ይገኝበታል።ከዚህ በተጨማሪ ኢምፔሪያል አካባቢ የመሰረት ድንጋይ ከተቀመጠ ከአስር ዓመት በላይ ያስቆጠረው እና እስካሁን በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታው ያልተጠናቀቀው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ሊያስገነባው ያሰበው ስታድየም የጉብኝቱ አካል ሲሆን፤ ጀሞ አካባቢ በቅርብ ዓመታት ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠለት የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ስታድየም በጉብኝት ሥነ ስርዓቱ ተካቷል።ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን የሚጎበኙ ሲሆን ምክትል ከንቲባው ከጉብኝቱ ባሻገር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ አቅጣጫ ያስቀምጣሉም ተብሎ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2011ቦጋለ አበበ ", "passage_id": "a7b7ce567bd6a47c3e4136e42f18ef20" }, { "passage": "በተለያዩ ቦታዎች ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ልምምድ ይሰራ የነበረው ኢትዮጵያ ቡና የራሱ የልምምድ ሜዳ አዘጋጅቶ ማጠናቀቁ ታውቋል።ለቡ (ጀሞ) በሚገኘው ክለቡ ለስታዲየም ግንባታ እንዲውል በተፈቀደለት ይዞታ ላይ ከወራት በፊት አቅዶ ወደ ሥራ ገብቶ የነበረው። ይልቁንም ያለፉትን ሦስት ወራት በተደረገው ከፍተኛ ጥረት በአሁኑ ሰዓት ቦታውን በጊዛዊነት ክለቡ ልምምድ እንዲሰራበት መጠናቀቁን ለማወቅ ችለናል። ምን አልባትም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ውድድሮች መሰረዛቸውን ተከትሎ እንጂ ክለቡ በቀጣይ ልምምድ ለመስራት ወደ ተለያዩ ቦታዎች የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በማቆም ራሱ ባዘጋጀው ቦታ ልምምድ እንደሚሰራ ታውቋል። ያለፉትን ዓመታት የራሱ የልምምድ ሜዳ ባለመኖሩ ምክንያት ለልምምድ ሜዳ ኪራይ በቀን ከሁለት ሺህ ብር በላይ ያወጣ የነበረ ሲሆን ይህ የልምምድ ቦታው መዘጋጀቱ ክለቡን ያወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ እንደሚቀንስ ታውቋል። ለጊዜው ለልምምድ ሜዳነት ይሰራ እንጂ በቀጣይ ኢትዮጵያ ቡና በሜዳው የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች በዚህ ሜዳ ለማድረግ ከወዲሁ ከፍተኛ ሥራ ይሰራል ተብሏል። ይህም ብቻ ሳይሆን የክለቡን ገቢ ለማሳደግ ሌሎች ክለቦች ልምምድ እንዲሰሩ እና የሚጫወቱበት ሜዳ እንዲሆን ጭምር ለማከራየት መታቀዱን ሰምተናል።በሌላ ዜና የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ሊያስገነባው አዲስ ስታዲየም ከከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን 7,723 ካሬ ሜትር ስፉት ያለው ቦታን ለማስጀመር አንዳንድ በአካባቢው ቀድመው የተገነቡ ህንፃዎች የፈጠሩትን ተግዳሮት ቀጣይ በምን መልኩ ማስተካከል ይገባል በማለት በትናትነው ዕለት የመስክ ምልከታ ተደርጓል። በመስክ ምልከታው ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አረጋይን ጨምሮ የንፋስ ስልክ ክ/ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የክፍለ ከተማው የመሬት ልማት ኃላፊ እና የወረዳው አመራሮች የኢትዮጵያቡና ስፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ፣ የክለቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ወልዴ እንዲሁም የደጋፊ ማኅበሩ አመራሮች ተገኝተዋል። በቦታው በተደረገው ምልከታ የሰታድየም ግንባታወን ለመጀመር በቦታው ላይ ያለየትን ችግሮች ለመቅረፍ ሰፊ ውይይት እንደተደረገ ሰምተናል።", "passage_id": "8492649899852fbe8dbaf746ef5f1086" }, { "passage": "በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው የስፖርት ሴክተር ዓመታዊ ጉባዔ ላይ የአዲስ አበባ ስታዲየም እድሳት ሊደረግለት እንደሆነ ተገልጿል።\nበኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አዘጋጅነት የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት ያካተተ የስፖርት ሴክተር ዓመታዊ ጉባዔ ዛሬ እና ነገ እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል። በጉባኤው ላይም የቀጣይ የሴክተሩ ስትራቴጂክ ዕቅድ፣ የ2012 ሪፖርት እና 2013 በጀት ዓመት ዕቅድ፣ የተሻሻለው የሀገር አቀፍ ስፖርት ማህበራት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ፣ የኮሮና ቫይረስን አስመልክቶ የተዘጋጀው የማገገሚያ ስትራቴጅክ ሰነድ እና የስፖርት ማህበራት መመዘኛ ስታንዳርድ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።በዛሬው ውሎም ኮሚሽኑ የአዲስ አበባ ስታዲየምን በ2013 ለማደስ ማቀዱን አስረድቷል። ንብረትነቱ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የሆነው ይህ አንጋፋ ስታዲየም ከካፍ በመጡ ገምጋሚዎች ለአህጉራዊ እና ዓለማቀፋዊ ውድድሮች ብቁ እንዳልሆነ መገለፁ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎ ስፖርት ኮሚሽኑ 25 ሚሊዮን ብር ለእድሳት በማውጣት ስታዲየሙን የማብቃት ስራ በ2013 እንደሚሰራ ጠቁሟል። ኮሚሽኑ በገለፃው ወቅት ለእድሳቱ አስፈላጊ ነው የተባለውን 25 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሚኒስቴር መፍቀዱንም አያይዞ አስረድቷል።ጥቅምት 23 ቀን 1940 የመሰረተ ድንጋይ የተጣለለት ይህ ዕድሜ ጠገብ ስታዲየም ሦስት የፍፃሜ ጨዋታዎችን ጨምሮ 31 የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎችን እና በርካታ አሕጉራዊ ውድድሮችን ማስተናገዱ አይዘነጋም።", "passage_id": "d140c51986bf101814849c1204f63f3a" }, { "passage": " እድሜ ጠገቡ የአዲስ አበባ ስታዲየም ከተማዋን በማይመጥን መልኩ በርካታ ጉዳቶች ያሉበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህም ምክንያት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍን) የስታዲየም መስፈርትን ያላሟላ በመሆኑ አህጉርና ዓለም አቀፍ ጨዋታዎችን እንዳያስተናግድ አግዶታል፡: ይህ ታሪካዊ ስታዲየም ደረጃውን የሚመጥን እድሳት ሊደረግለት እንደሚገባ በብዙዎች ሲነሳ ቆይቷል፡፡ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ስታዲየሙ እድሳት ሊደረግለት መሆኑን አስታውቋል፡፡ እድሳቱን ለማከናወንም የዲዛይን፣ የማማከር እና የቁጥጥር አገልግሎት ከሚሰራ ድርጅት ጋር የውል ስምምነት ተደርጓል። ስራውን የሚያከናውነውም ዮሐንስ አባይ የተባለ አማካሪ አርክቴክቸር እና ኢንጅነሪንግ ድርጅት ሲሆን፤ የዲዛይን ስራውን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅም ይታወቃል። እድሳቱ የካፍ መስፈርትን ጠብቆ የሚሰራም ነው።", "passage_id": "a606ead7eb20c665dbc2d14c054e6395" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ከሌሶቶ ብሄራዊ ቡድን ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ዝግጅቱን ቀጥሏል፡፡የዋልያዎቹን የመጨረሻ የማጣርያ ጨዋታ በአምበልነት የመራው ሽመልስ በቀለ ትላንት አዲስ አበባ የገባ ሲሆን በዛሬው እለትም ከቡድኑ ጋር የመጀመርያ ልምምዱን ሰርቷል፡፡ ጌታነህ ከበደ ደግሞ ዛሬ አዲስ አበባ የሚገባ ሲሆን ነገ ከቡድኑ ጋር ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡የብሄራዊ ቡድኑ ጥሪ ከደረሳቸው 25 ተጫዋቾች መካከልም 24ቱ ልምምዳቸውን ሲሰሩ በጠባብ ሜዳ ውስጥ ክፍተት የማግኘት እና ጎል የማስቆጠር ልምምዶች እንዲሁም  ለሁለት ተከፍለው መጫወት የዛሬ የልምምዳቸው አካል ነበር፡፡ብሄራዊ ቡድኑ ኢንተርናሽናል የአቋም መለኪያ ጨዋታ ያላገኘ ሲሆን በነገው እለት ጠዋት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ እንደሚያደርጉ ታውቋል፡፡አሰልጣኝ ገብረመድን እስካሁን ባለው ዝግጅት በጣም ደስተኛ እንደሆኑና በቡድኑ ቅንጅትና እንቅስቃሴ እንደተገረሙ እና ጥሩ ስራ እየሰሩ መሆኑን ለሶከር ኢትዮዽያ ተናግረዋል፡፡ዋልያዎቹ በዕለተ ረቡዕ ወደ በደቡብ አፍሪካ ትራንዚት አድርገው ሌሶቶ የሚያመሩ ሲሆን እሁድ ግንቦት 28 ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ሶከር ኢትዮዽያ ነገ በብሄራዊ ቡድኑ ዝግጅት ዙርያ የተጨዋቾችን እና አሰልጣኞች አስተያየት ይዛ የምትቀርብ ይሆናል፡፡", "passage_id": "be052208daacb396fcc5010fb949e8a7" } ]
ab832e0c93d1c02de1ab3a22c9255d34
c6207ecebf17188361e6c7e2c5b878b9
“የጉዳዮችመዘግየትና ተደጋጋሚ ቀጠሮዎች የፍትህ ተቋማቱ ያልተሻገሯቸው ችግሮች ናቸው”አቶ ፉአድ ኪያር የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት
እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ የጉዳዮች መዘግየትና ተደጋጋሚ ቀጠሮ የፍትህ ተቋማት ያልተሻገሩትና እስከ አሁንም ድረስ አብሯቸው የቀጠለ ችግር መሆኑን የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተናገሩ፡፡ፕሬዚዳንቱ አቶ ፉአድ ኪያር ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ ቀልጣፋ የፍትህ አሰጣጥ፣ የጊዜ ቀጠሮ ማሳጠርና ሌሎች የፍትህ ሂደቶች ከለውጡ በፊትም ሆነ በኋላ የፍትህ ተቋማት በፍትህ ስርዓቱ ላይ መሻገር ካልቻሏቸው ነገሮች መካከል ይጠቀሳሉ።ለዚህ ችግር መሰረታዊ መፍትሔ ማምጣትና መሻገር የሚቻለው ደግሞ፣ አንድ ጉዳይ መቼ ተጀምሮ በምን ያህል ጊዜ ማጣራትና ክርክር ከተደረገበት በኋላ መጠናቀቅ አለበት በሚለው ላይ ቀመር አውጥቶ ከዳኞች በመግባባት ምክንያታዊ ጊዜ ሰጥቶ እንዲያልቁ ማድረግ ሲቻል ነው፡፡እንደ አቶ ፉአድ ገለጻ፤ የወንጀል ጉዳዮች ፍርድ ቤት ላይ ተጀምረው እዛው የሚያልቁ አይደሉም።ይልቁንም የሌሎች የወንጀል ፍትህ አስተዳደር አካላትን ቅንጅታዊ አሰራር ስለሚፈልጉ ናቸው።አንድ የወንጀል ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ሲውልም ከፖሊስ ጀምሮ አቃቤ ህግ፣ ፍርድ ቤት በመጨረሻም ማረሚያ ቤት በሂደቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት ነው።ለምሳሌ፣ ተከሳሹን በማቅረብ ጥራቱን የጠበቀ ምርመራ በመስራት ክሱን ጥርት አድርጎ በማቅረብና በፍርድ አሰጣጥ በኩል ከፍተኛ የሆነ የቅንጅት ስራ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች ላይ የሚሰጠው የጊዜ ቀጠሮ መራዘም በፍርድ ቤት የስራመጓተት ብቻ ሳይሆን ፖሊስ በቶሎ ምርመራውን ያለመጨረስ߹ አቃቤ ህግ ጉዳዩን በቶሎ ወደፍርድ ቤት ያለማምጣት߹ ፍርድ ቤት ከመጣ በኋላ ደግሞ ጉዳዮች በቶሎ እልባት የሚያገኙበት የተቀመጠ የጊዜ ገደብ አለመኖር߹ መዝገብ ምስክር ማስረጃና ሌሎች ነገሮችም አልቀረቡም በማለት በተደጋጋሚ በሚሰጥ ቀጠሮ ምክንያት መዘግየቶችና ተደጋጋሚ ቀጠሮዎች እንደሚያጋጥሙ ነው አቶ ፉአድ የገለጹት፡፡በዚህ ረገድ የፍርድ ቤትን ድርሻ ወስደን የዘገዩ መዝገቦች ቅድሚያ አግኝተው እንዲሰሩ አልተመረመረም የሚባል መዝገብ እንዳይኖር ለማድረግ አብዛኞቹ ዳኞች ረዳቶች እንዲኖሯቸው ተደርጓል ያሉት አቶ ፉአድ፤በዚህም ለውጦች እየመጡ በመሆኑ ይህ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስረድተዋል፡፡በሌላ በኩል ደግሞ የባለጉዳይ መስተንግዶ በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ዘንድ እንደ ችግር የሚነሳ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ፉአድ፤ እንዴት ነው ባለጉዳይ የምናስተናግደው? የሚለው ከሰራተኛው ጀምሮ እስከ ዳኛ ድረስ የሚሄድና መስተካከል ያለበት እንደሆነም ገልጸዋል።በዚህ በኩል ያሉ ችግሮችንም ለይቶ በጥራት በቅልጥፍናና በውጤታማነት ለመስራት የተለያዩ ሙከራዎች መኖራቸውን አብራርተዋል፡፡እንደ አቶ ፉአድ ገለጻ፤ እንደመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የመዝገቦች መዘግየትን ለማጥፋት እድሜያቸው አንድ ዓመትና ከዛ በላይ ያስቆጠሩ መዝገቦች ላይ ልክ እንደ መኪና ታርጋ “የዘገየ” የሚል በመለጠፍ ዳኞች ከምንም ጉዳይ በፊት ቅድሚያ ሰጥተው እንዲያዩና እልባት እንዲሰጡ በማድረግ ባለፈው ዓመት ብቻ ከ 6ሺ 800 በላይ የሚሆኑ የተከማቹ መዝገቦችን እልባት መስጠት ተችሏል። በዚህም አንድ አመትና ከዛ በላይ የቆዩ መዝገቦች ተቃለዋል።ይህም ሆኖ ግን በየቀኑ የሚከፈቱ መዝገቦች ስላሉ ችግሩ ይቃለል እንጂ የመዝገቦቹ ብዛት እንዳለ ነው፡፡በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ያሉበትን ችግሮች ለመቅረፍ “የኬዝ ፍሎው ማኔጅመንት” አሰራርን ለመከተል ያቀደ መሆኑን በመጥቀስ፤ ለምሳሌ፣ አንድ በስርቆት ወንጀል የተጠረጠረን ግለሰብ ክስ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በአራት ወር ውስጥ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ለማድረግ እና ከዚህ ጊዜ በላይ የሚጠይቁ ወንጀሎችን ደግሞ ታሳቢ በማድረግ ስራዎች እንደሚሰሩም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37863
[ { "passage": "የህግ የበላይነትንና ፍትህን ለማስፈን የፌዴራል መንግሥት ለክልሎች በውክልና የሰጠውን የከፍተኛና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በማንሳት በአገሪቱ በሙሉ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ማዋቀር እንደሚገባ ምሁራን ይገልጻሉ። በህገ መንግሥቱ አንቀጽ 78 ንዑስ አንቀጽ 2 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የፌዴራል ከፍተኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶችን በአገሪቱ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲያደራጅ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ሊወስን እንደሚችል ያስቀምጣል። በዚህ ረገድ አንዳንድ የህግ ምሁራን ፍትህን ለማስፈን የመጀመሪያና የከፍተኛ ፍርድ ቤቶች በአገር አቀፍ ደረጃ መቋቋም አለባቸው ይላሉ። ሌሎች ምሁራን ደግሞ የስልጣን ውክልናውን ማስቀጠል ፍትህንና የህግ የበላይነትን እንደሚያሰፍን ያመላክታሉ። የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል መስሪያ ቤታቸውን የዘጠኝ ወር ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርቡ ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በማፈናቀል አራት ሺህ 43 መዝገቦች ላይ ምርመራ ተደርጎ በሁለት ሺህ 276ቱ ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት ተልኳል። ክስ የተመሰረተባቸው አራት መቶ 68ቱ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ አፈናቃዮች በህግ ጥላ ስር አልዋሉም። ለዚህም ዋናው ምክንያት አፈናቃዮችን ለማቅረብ በየደረጃው የሚገኝ የፖለቲካና የጸጥታ አመራር ቁርጠኛነትና አለመተባበር ነው ብለዋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም በአገሪቱ የፍትህ አሰጣጥ ሂደት መጓደል አለ። የህግ የበላይነት ማስከበር ችግር ላይ እየወደቀ ነው። የክልል ፍርድ ቤቶችም በተሰጣቸው የፌዴራል የዳኝነት ውክልና ለዜጎች ገለልተኛ ሆነው ፍትህ እየሰጡ አይደለም ብለዋል፡፡ በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የህግ መምህሩ ረዳት ፕሮፌሰር ለገሰ ጥጋቡ፤ የህግ የበላይነትና ፍትህን ለማስፈን የፌዴራል መንግሥት ያወጣቸው ህጎች በፌዴራል ፍርድ ቤቶች መዳኘት አለባቸው። ይህ ባለ መሆኑ ወንጀለኞች ክልሎችን እንደመጠጊያ እየተጠቀሙ ነው። ዜጎችም በገለልተኛነት ፍትህን ማግኘት አልቻሉም። የህግ የበላይነትን ለማስከበርም አልተቻለም። ስለሆነም፤ የፌዴ ራል መንግሥት በውክልና ለክልሎች የሰጠውን ስልጣን በመመለስ ፍርድ ቤቶችን በክልሎች አደራጅቶ ፍትህን ለተጠማው ህዝብ መስጠት አለበት ይላሉ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው የህግ መምህር ዶክተር መሀሪ ረዳኢ፤ የረዳት ፕሮፌሰሩን ሃሳብ አይቀበሉም። እርሳቸው እንደሚሉት፤ የፌዴራል መንግሥት ውክልናውን ከማንሳት ይልቅ ፍትህ ማጣት አገርን ያጠፋል በሚል ዕምነት ተቀራርቦ መስራት፤ የጋራ አመለካከት መፍጠር፤ በፍትህ ዘርፉ ያለውን ችግር አንጥሮ በማውጣት መፍትሄ መስጠት፤ መርህና ህግን መሰረት ያደረገ ዘላቂ መፍትሄ መፈለግ እንደሚገባ ያመላክታሉ። የክልሎችን ውክልና አንስቶ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን በአገሪቱ ክልሎች ማደራጀት ልዩነት የለውም። በክልሎች ያሉ ዳኞች ችግር በፌዴራል አለ። ከብሄርም አንፃር ስልጣን የሚያገኙት ከክልሎች ስለሆነ ብሄርተኞች ናቸው። ውክልና ቢነሳም በሚቋቋሙት ፍርድ ቤቶች የሚመደቡት ዳኞች የአካባቢውን ቋንቋ መቻል ስላለባቸው የዚያው አካባቢ ሰዎች ናቸው። ፍትህ ካጓደሉ ውክልናው ተነስቶም ቢሆን ያጓድላሉ። ሁሉም ተባብሮ ከመስራት ባለፈ ውክልናውን ማንሳት በፌዴራል እና በክልሎች መካከል አለመተማመን ከመፍጠር ያለፈ ፋይዳ የለውም ባይ ናቸው። ረዳት ፕሮፌሰር ለገሰ ለዶክተር መሀሪ አስተያየት ምላሽ አላቸው። እርሳቸው እንደ ሚሉት የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በአገሪቱ መደራጀታቸው ክልሎችን መጠጊያ የሚያደርጉ ወንጀለኞችን ትክክለኛ ፍርድ ይሰጣል። ህጎቹ የፌዴራል ስለሆኑ የፌዴራል የዳኝነት አካሉ በህጉ መሰረት ፍትህ ይሰጣል። አስተዳዳሪውም ፌዴራል ስለሆነ ያለ ጫና ገለልተኛ ሆነው ይወስናሉ። ፍርድ ቤቶች ከክልል ባለስልጣናት ተጽዕኖ ነፃ ሆነው ለመስራት በፌዴራል መንግሥት ቢደራጁ የተሻለ ነው። 80 በመቶ የአገሪቱን በጀት የሚያስተዳድረው የፌዴራል መንግሥት ስለሆነ ችግሩን ለመቅረፍና ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር የተሻለ ዕድል አለ። የህግ ምሁር አቶ ሙልዩ ወለላው፤ አገሪቱ አሁን ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ በፌዴራል መንግሥት ስልጣን ስር የሚወድቀውን የፍርድ ቤት ስልጣን የፌዴራል መንግሥት ፍርድ ቤቶችን በመላ አገሪቱ አዋቅሮ ቢመራ መልካም መሆኑን ያነሳሉ። ሀሳባቸውን በምክንያት ሲያስደግፉም፤ በፌዴራል ስልጣን ስር የሚወድቁ የዳኝነት ሥራዎች በክልሎች የመፈጸም ችግር እየገጠማቸው ነው። አንፈጽምም ባይሉ እንኳን የማጓተት ሁኔታ ይታያል። በህገ መንግሥቱ የተቀመጠው የስልጣን ኃላፊነት አሁን ላይ እየተደበላለቀ ነው። የአገልግሎት አሰጣጥ መጓተትም በክልል ፍርድ ቤቶች ይታያል። ከዚህም በላይ በአሁኑ ወቅት ክልሎች «በእኔ ክልል አትግባ» በሚሉበት ወቅት በፌዴራል ስልጣን ስር የሚወድቁ የዳኝነት ኃላፊነቶች በትክክል ተግባራዊ ማድረግ አይቻልም። በዚህም የዜጎች ፍትህ የማግኘት መብት እየተጓደለ ነው። የፍርድ ቤቶችን አስተዳደራዊ ነፃነት ለመጠበቅ እና በፋይናንስ ጠንካራ ለማድረግ የፌዴራል መንግሥት በአገሪቱ ፍርድ ቤቶችን ቢያዋቅር የዳኝነት ስርዓቱ ውጤታማ ይሆናል። ነገር ግን፤ ወደ ሥራ ከመገባቱ በፊት ግምገማዊ ጥናት አድርጎ ችግሩን መፈተሽና መፍትሄ ማመላከት የተሻለ መሆኑንም አመላክተዋል። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚ ዳንት ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ፤ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ባዘጋጀው «አዲስ ወግ» በተባለው የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የህግ የበላይነትን በማስከበር ረገድ ደረጃዋ ዝቅተኛ ነው። እ.ኤ.አ በ2018 የዓለም አቀፉ ፍትህ ፎረም ባወጣው ሪፖርት ከዓለም ከ126 አገራት 118ኛ ስትሆን በአፍሪካ ከ30 አገራት 27ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በተመሳሳይ ወቅት የሰዎች ነፃነት ፎረም የተባለው ድርጅትም በአገሪቱ የህግ የበላይነት ከ162 የዓለም አገራት 150ኛ መሆኗን ማረጋገጡን አመላክተዋል። ይህ የፕሬዚዳንቷ መረጃ ኢትዮጵያ በህግ የበላይነትና ፍትህን በማስፈን ወደኋላ መቅረቷን ያመለክታል። ፕሬዚዳንቷ፤ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በርካታ ተቋማት ሚና አላቸው። ዋናዎቹ ፍርድ ቤቶች ናቸው። ፍርድ ቤቶች ግን ደካማ ናቸው። የህግ የበላይነት እንዲከበር በፍትህ አካላት ተዕልኮና ሚና ላይ የጋራ መግባባት አልነበረም። ተቋማቱና መሪዎቹ ነፃ አልነበሩም። የተነሳሽነትና የሀብት ውስንነት አለባቸው። ፍርድ ቤቶች የተገልጋዩን ብዛት የሚመጥን አቅም የላቸውም። በአጠቃላይ ፍርድ ቤቶች መቀየር አለባቸው ይላሉ። በምሳሌም ሲያመላክቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዓመት 15 ሺህ፤ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 20 ሺህ፤ እንዲሁም የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 140 ሺህ ጉዳዮች ለማስተናገድ ያቅዳሉ። ከእቅዱ በተቃራኒው ዳኞች ቀጠሮ አስይዘው ማስቻያ ስለሌላቸው ቀጠሮ ያስቀ ይራሉ። ማስቻያ በማጣታቸውም ዳኞች በሳምንት ሁለት ቀን ብቻ ፍርድ እንደሚሰጡ በማንሳት አንገብጋቢ ችግር መኖሩን ያስረ ዳሉ።በአገሪቱ ያለው የፍትህ ስርዓት በብዙ ችግር ውስጥ እንደሆነ በሁሉም ደረጃ የሚታመን ሀቅ ነው። ችግሩም ከመዋቅር አንስቶ እስከ ግለሰብ ባለሙያ የሚደርስ ነው። ይህን ለመፍታትም በጥናት ላይ ተመስርቶ ችግሮችን መለየት አስቻይ ሁኔታዎችን ማወቅና በጥናቱ ውጤት ላይ ተመስርቶ ፍርድ ቤቶችን በፌዴራል በማዋቀር ወይም በነበረው የውክልና አካሄድ ጠንካራ የፍትህ ስርዓት መዘርጋት ለነገ የሚባል ሥራ አይደለም።አዲስ ዘመን ግንቦት 7/2011 በአጎናፍር ገዛኸኝ ", "passage_id": "e1d0cd96855bf9015def8d72bd085d5d" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- በ2012 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት 90ሺ ጉዳዮች ውሳኔ ማግኘታቸውን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ገለጹ፡፡ የፌዴራል ዳኞች ወርሃዊ የእርስ በርስ መማማሪያ መድረክ ተካሄደ፡፡ የመማማሪያ መድረኩ\nከትናንት\nበስቲያ\nሲካሄድ\nየጠቅላይ\nፍርድ\nቤት\nፕሬዚዳንት\nወይዘሮ\nመዓዛ\nአሸናፊ\nእንደገለጹት፤\nየፌዴራል\nዳኞች\nባለፉት\nስድስት\nወራት\nብቻ\nለ90ሺ ጉዳዮች ውሳኔ\nሰጥተዋል።\nይህም\nየእቅዱን\n104 በመቶ\nነው።\nዳኞች\nሕዝብን\nበትህትና\nበማገልግልና\nጥራት\nያለው\nውሳኔ\nለመስጠት\nበተቻላቸው\nአቅም\nጥረት\nእያደረጉ\nመሆኑን\nየገለጹት\nፕሬዚዳንቷ፤የፌዴራል\nዳኞች\nሕግን\nመሠረት\nአድርገው\nበነፃነትና\nበትህትና\nሕዝብን\nእያገለገሉ\nመሆኑን\nአመልክተዋል፡፡ እንደ\nወይዘሮ መዓዛ ገለጻ፤\nጠቅላይ ፍርድ ቤቱ\nየፍርድ ቤቶችን አሠራር\nአቅም ለማሳደግና ለመለወጥ\nየሦስት ዓመታት የማሻሻያ\nሥራዎችን እየቀረጸ ነው።\nለሕዝብ ተወካዮች ምክር\nቤትም ሁለት የሕግ\nማሻሻያዎች ልኳል። የፍትህ ሥርዓቱን ለማሻሻል እየተሰራ ነው ያሉት ወይዘሮ መዓዛ፤ ዳኞችም ሥራቸውን በጥራት በማከናወን ኅብረተሰቡን ከጎናቸው በማድረግ አገልግሎታቸውን የበለጠ ማሳደግ እንደሚገባቸው አመልክተዋል።በወርሃዊ የእርስ በርስ መማማሪያ መድረኩ ላይ በካሊፎርኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ምሁሩ ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም፤ «ሕገ መንግሥትና ፍርድ ቤቶች» በሚል ርዕስ የመወያያ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ፕሮፌሰሩ፤ በሰጡት ማብራሪያ ፍርድ ቤቶች የሕገ መንግሥቱ ጠባቂ ናቸው። ያለ ፍርድ ቤቶች ጥብቅና ሕገ መንግሥቱ አይኖርም። ከምክር ቤት በአብላጫ ድምጽ የሚመጡትን የፖለቲካል ውሳኔዎች ሕግ ከመሆናቸው በፊት ፍርድ ቤቶች በሕገ መንግሥቱ በማንጸር እንዲወጡ ያደርጋሉ። ይህም በአንድ አገር ውስጥ ዴሞክራሲ፣ ነፃነት፣ ፍትህና እኩልነትና ሌሎች መብቶች እንዲኖሩ ያደርጋሉ። ዳኞች ለሕገ መንግሥቱ መጠበቅና ለሕግ የበላይነት መረጋገጥ የማይተካ ሚና አላቸው። በአንድ አገር ውስጥ ዳኞች ሥራቸውን በነፃነትና በአግባቡ ካልሰሩ ፍትህ እናመጣለን ማለት መፈክር ብቻ መሆኑን ተናግረዋል።የዳኞች ኃላፊነት ሸክም ነው ያሉት ፕሮፌሰሩ፤ ሥራቸውን በሰብዓዊነት፣ በተስተካከለ ህሊና፣ በላቀ እውቀትና አስተሳሰብ፣ በሞራል ልዕልና፣ በሩቅ አሳቢነትና ሁሉን አካታች በሆነና በፍትሀዊነትና በጥልቀት በመመርመር አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ተሳታፊ ዳኞች «በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥቱን የመተርጎም ሥልጣን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት» መሰጠቱን በማንሳት አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት ፕሮፌሰር አለማየሁ፤ ሕገ መንግሥቱ በተለያየ አገር በተለያየ አካላት ይተረጎማል። ሆኖም ከአስፈፃሚው ጋር መደረብ የለበትም። ገለልተኛ መሆን አለበት። በኢትዮጵያ ይህ እንዲሆን ዳኞች ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጋር ተቀራርቦ መወያየት። የሕግ ፕሮፌሰሮችና የሕግ ባለሙያዎች ጋር አብሮ በመሆን የአሁኑን አካሄድ በጥልቀት መመርመር፣ ሁሉን አሳታፊ በሆነ መንገድ በመወያየት መፍትሄ ማምጣት እንደሚቻልም መክረዋል።አዲስ ዘመን ካቲት 8/2012አጎናፍር ገዛኸኝ", "passage_id": "5c2c8fab80ab0cfcc0517ff5a96c0706" }, { "passage": "በዳኝነት ነፃነት ላይ ጣልቃ መግባት እንዳይሆን ተሠግቷልየፍትሐ ብሔር ውሳኔዎች በማኅበራዊ ትስስር ገጽ እንዳይገለጹ ታገደበፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ከሚታዩ የክስ መዝገቦች ውስጥ በክርክርና በቀጠሮ ላይ ያሉ መዛግብት፣ ከመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. በኋላ ባሉት ጊዜያት እንዲቀጠሩ ለየምድብ ችሎቶቹ ማሳሰቢያ መሰጠቱ ተጠቆመ፡፡ ማሳሰቢያው የተሰጠው በፍርድ ቤቱ አመራሮች በመሆኑ፣ በዳኝነት ነፃነት ላይ ጣልቃ መግባት እንዳይሆን የሕግ ባለሙያዎች ሥጋታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ፍርድ ቤቱ በክርክር ላይ ያሉ ወይም ክርክራቸው የተወሰነ ጊዜ የሚወስድ መዛግብት ለቀጣዩ ዓመት ከመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. በኋላ እንዲቀጠሩ አመራሩ የገለጸ ቢሆንም፣ የኮሮና ወረርሽኝ በኢትዮጵያ ያለው ሥርጭት ከተቃለለ፣ የቀጠሮ ጊዜ ተሰብሮ በነሐሴ ወር 2012 ዓ.ም. ሊሠራ እንደሚችልም አማራጭ ሐሳብ አስቀምጧል፡፡ የፍርድ ቤቱ አመራር ያስተላለፈውን ማሳሰቢያ በሚመለከት አስተያየታቸውን የሚሰጡ የሕግ ባለሙያዎች እንደገለጹት፣ አመራሩ የሰጠውን ማሳሰቢያ በሁለት ከፍለውታል፡፡ የመጀመርያው ከተከሳሹ የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብት አንፃር ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተሠራጭቶ ከሚገኘው ኮሮና ቫይረስ አደገኛ ሁኔታ አንፃር ነው፡፡ በእስር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች ቤተሰቦችና ሌላ የችሎት ታዳሚዎች በሌሉበት ርቀታቸውን በጠበቀ ሁኔታ ክርክር በማድረግ አንድ ደረጃ ላይ መድረስ እየቻሉ፣ ሙሉ በሙሉ መከልከል ግን የመብት ጥሰት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል የፍርድ ቤቱ አመራር በወረርሽኙ ይከሰታል ብሎ የሚሠጋበትን ጉዳት የሚያሳይ በመሆኑ፣ ማሳሰቢያው ተገቢ መሆኑንም የሚደግፉ የሕግ ባለሙያዎች አሉ፡፡ በሌላ በኩል አንድ ዳኛ በያዘው መዝገብ ላይ የመወሰንና የማዘዝ ሥልጣኑ የዳኛው ሆኖ ሳለ፣ ‹‹ይህንን አድርግ›› ማለት በዳኝነት ነፃነት ላይ ጣልቃ መግባት በመሆኑ እንዳሳሰባቸውም ገልጸዋል፡፡ የሕግ ባለሙያዎቹ ከመብት ጥሰትና በዳኞች ነፃነት ላይ ጣልቃ መግባት ላይ ባነሱት ጥያቄ፣ ፍርድ ቤቱ የክርክርና የቀጠሮ መዛግብትን ከመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. በኋላ ለምን መቅጠር እንደፈለገ ምላሽ እንዲሰጡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃነ መስቀል ዋጋሪ፣ ፍርድ ቤት አልተዘጋም ብለዋል፡፡ ‹‹ሕዝብ ፍትሕ ማግኘት አለበት፡፡ ፍትሕ እንደ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ ውኃና ሌሎች መሠረታዊ ነገሮች ነው፡፡ ነገር ግን ዓለም አቀፉ ኮሮና ወረርሽኝ በኢትዮጵያም በመከሰቱ፣ የሕዝብ መሰባሰብን ማለትም ችሎት ለመከታተል፣ ዋስ ለመሆን፣ ለዋስትና ያስያዙትን ገንዘብ ለመውሰድ፣ የውሳኔ ግልባጭ ለመውሰድና ለሌሎች ጉዳዮች ወደ ፍርድ ቤት የሚመጣውን ማኅበረሰብ ለማስቀረት ፍርድ ቤት በከፊል እንዲዘጋ ተደርጓል፤›› ብለዋል፡፡ ለወረርሽኙ መስፋፊያ ከሆኑት ምክንያቶች አንዱ መሰባሰብ በመሆኑ፣ ያንን ለማስቀረትና የሚደርሰውን አደጋ ለመቀነስ እንጂ ሌላ ምክንያት እንደሌለው አክለዋል፡፡ በጣም አስፈላጊና አስቸኳይ የሆኑ የወንጀልም ሆነ የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች በተረኛ ችሎቶች እንደሚታዩ ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል፡፡ የወንጀል ክስ ኖሮባቸው በማረሚያ ቤት ያሉ ተጠርጣሪ ታሳሪዎች ጉዳይ ባሉበት ቦታ በቴሌ ኮንፈረንስ ለማከራከር ዝግጅቶች እየተሟሉ መሆኑን፣ አቶ ብርሃነ መስቀል ተናግረዋል፡፡ እንደ ወረርሽኙ ሁኔታ ፍርድ ቤቶች ሙሉ በሙሉ የሚዘጉበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ፣ መታሰብ ያለበት ግን ሲከፈት ምን ያህል ባለጉዳይ ፍርድ ቤቶችን ሊያጥለቀልቅ እንደሚችል መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቶቹ ሙሉ በሙሉ ሳይዘጉ እንዴት መቀጠል እንዳለባቸው ከችሎት አስተባባሪ ዳኞች ጋር በተደረገ ውይይት አንድ የውሳኔ  ሐሳብ ላይ መደረሱን ጠቁመው፣ የችሎት አስተባባሪ ዳኞች ከችሎት ዳኞች ጋር በመወያየትና የዳኞቹን ውሳኔ በማወቅ፣ ችሎቶች ሳይሠሩ የሚቀጥሉበትን ማመቻቸት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡የችሎት ዳኞችን ባገኙት መገናኛ ዘዴ ያነጋገሩት የችሎት አስተባባሪዎች ያገኙት ምላሽ፣ ሰኔ መጨረሻና ሐምሌ መጀመርያ አካባቢ ወረርሽኙ በስፋት ይሠራጫል የሚል ሥጋት ስላለ፣ እስከዚያው ድረስ የክርክርና የቀጠሮ መዝገቦችን ረዘም አድርጎ በመቅጠር ጊዜው በሰላም ካለፈ፣ ነሐሴ 2012 ዓ.ም. እና መስከረም ወር 2013 ዓ.ም. ለመሥራት ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች የሚያዩዋቸው ጉዳዮች ከባድና ትልልቅ በመሆናቸው፣ እንዲሁም ዳኞቹ ከፍተኛ የሆነ ልምድ ያላቸው ስለሆኑ እነሱ ያልመከሩበት ውሳኔ ሊተላለፍ እንደማይችል የገለጹት አቶ ብርሃነ መስቀል፣ አንድ ዳኛን እንኳን ‹‹ይህን መዝገብ ሥራ፣ ያንን መዝገብ ተው›› ብሎ ጣልቃ በመግባትና ማዘዝ ቀርቶ ስለያዘው መዝገብ እንኳን ማንሳት እንደማይቻል አስታውቀዋል፡፡ ማንም አካል በዳኝነት ነፃነት ላይ ሊገባ እንደማይችልም አክለዋል፡፡ የፍርድ ቤቱ አመራር ባደረገው ውይይት የደረሰበት ስምምነት፣ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጅ ጋር ተያይዞ፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ የሚቀርቡ ጉዳዮችን የማየት ሥልጣን የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት መሆኑን የፍርድ ቤቱ አመራሮች ገልጸዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የተረኛ ችሎት ዳኞችን ቁጥር በመጨመር በሚቀርቡ ጉዳዮች ላይ አፋጣኝ ምላሽ ይሰጣል፡፡ በተጨማሪም በሌሎች መዝገቦች ማለትም ለውሳኔ፣ ለብይንና ለትዕዛዝ የተቀጠሩ በርካታ የወንጀል መዛግብትና ውስን የፍትሐ ብሔር ጉዳዮችን ሥራ ማቃለል እንደሆነም በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ የፍርድ ቤቱ አመራር ሌላው ያስተላለፈው ሐሳብ፣ ፍርድ ቤቱ በከፊል ዝግ ከተደረገ በኋላ የፍትሐ ብሔር የውሳኔ መዝገቦች በፍርድ ቤቱ ማኅበራዊ የትስስር ገጽ ላይ እንዲወጡ የተወሰነ ቢሆንም፣ አመራሩ እንዲቆም ወስኗል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የተወሰነበት ወገን በወቅቱ ይግባኝ ማለት ስለማይችልና የፍርዱን ግልባጭ ማግኘት ስለሚቸገር፣ ሁሉም ሰው ማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ማግኘት ስለማይችል፣ የተወሰነለትም በወረርሽኙ ምክንያት ማስፈጸም ስለማይችል መታገዱን አቶ ብርሃነ መስቀል አስረድተዋል፡፡ውሳኔ ያረፈባቸው መዛግብት በዳኞች እጅ በመሆናቸው ሰብስቦ ወደ መረጃ ቋት (ዳታ) ማስገባትም ስለማይቻል መሆኑን፣ በርካታ ምክንያቶች እንዳሉም አክለዋል፡፡ ነገር ግን በልዩ ሁኔታ የልጅ፣ የቤተሰብ ቀለብ፣ የአሠሪና የሠራተኛ ጉዳይ፣ የጉዳት ካሳ፣ የሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የንግድና ኢንቨስትመንት፣ በአጠቃላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ አንድምታ ያላቸው ጉዳዮችና አስቸኳይ ጉዳዮች ከሆኑ ሊታዩ እንደሚችሉ የፍርድ ቤቱ አመራር ስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል፡፡ በማረሚያ ቤት ሆነው የጥፋተኝነት ፍርድም ሆነ ወይም የቅጣት ውሳኔ፣ በነፃ የሚለቀቁ ወይም እንዲከላከሉ ብይን የመሥራት ሥራ በሚገባ እንዲሠራና ውጤቱ እንዲነገራቸውም አመራሩ ተስማምቷል፡፡ በክርክር ሒደት ላይ ያሉት ደግሞ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ክርክር እንዲያደርጉና ፍትሕ እንዲያገኙ ለማድረግ አመራሩ ተስማምቷል፡፡ ስምምነቱ በቂሊንጦ፣ ቃሊቲ፣ ድሬዳዋና በክልል ያሉ ተዘዋዋሪ ችሎቶችን ያካተተ ነው፡፡ ከማረሚያ ቤት ውጪ በዋስትና ያሉ መደበኛ ችሎቶች እስከሚጀምሩ ድረስ ባሉበት እንደሚቆዩም ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩ መዛግብት በትብብር ተሠርተው እንዲጠናቀቁ፣ ለግንቦት ወር 2012 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጥቷቸው የነበሩ በከፊል ዝግ መሆኑን ያልሰሙ ባለጉዳዮችን፣ ዳኞች ከቻሉና ከፈለጉ ርቀታቸውን ጠብቀው ፍርዱን መንገር እንደሚችሉም ሐሳብ ሰጥተዋል፡፡ የዋስትና ገንዘብ ተመላሽ ማድረግ በሚመለከት በጣም የተቸገሩ ከሆነ እንደ ሁኔታው ዳኞች በሚሰጡት ትዕዛዝ እንዲፈጸምላቸው ተስማምተዋል፡፡ የየራሳቸውን ውዝፍ መዝገብ ሠርተው ያጠናቀቁ ዳኞች በፍርድ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች ፊት ዕውቅና እንደሚሰጣቸው፣ ያላጠናቀቁ ደግሞ የየራሳቸው ምክንያት ስለሚኖራቸው ሪፖርት እንዲያደርጉ አመራሩ መስማማቱ ታውቋል፡፡ ", "passage_id": "27cee6f3a44fe700997aae6cb6c6b214" }, { "passage": "በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና በዳኞችና ታዛቢዎች ማኅበር መካከል እየተካሄደ በሚገኘው ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረገው ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ዳዊት አሳምነው የስራ አስፈፃሚ አባል እና ሊግ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አበበ ገላጋይ ለዳኞች ስራ እንቅፋት መሆናቸውን ገልጿል።” ዳኞች ውሳኔ ለመወሰን የተቀመጠላቸው መስፈርቶች አሉ።  ለምሳሌ ተጫዋች በጨዋታ ላይ ሲያጠፋ የሚሰጠው የማስጠንቀቂያ ቢጫ ካርድ ወይም ቀይ ካርድ ዳኛው ሲሰጥ የተቀመጡ ሰባት መስፈርቶች አሉ። በእነዚህ መስፈርቶች መሰረት ቀይ ካርድ ወይም ቢጫ ካርድ እንሰጣለን። ሆኖም ይህ እየተሻረ ነው። አንድ ተጫዋች አራት ጨዋታ በቀይ ካርድ ምክንያት ተቀጥቶ በማግስቱ በምን መልኩ ቀይ ካርዱ እንደሚነሳ አናቅም። አንዳንድ ተጨዋቾች እንድያውም ቀይ ካርድ ስንሰጣቸው ” ችግር የለውም አንተ ቀይ ካርድ ብትሰጠኝ ነገ የሚያነሳልኝ አካል አለ” እያሉ ያፌዙብናል። ይሄን የሚያነሳው ሰው እዚህ የለም ቢኖር ጥሩ ነበር። ይህን የሚያደርገው የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ አቶ አበበ ገላጋይ ነው። ክለቦች እንዳይጎዱ እያለ ፤ ስለዚህ ይህ መቅረት አለበት ፊፋ ያስቀመጠው ህግ መከበር አለበት ። ” ብሏል።\n” ይህ የዳኛ ውሳኔ በግለሰቦች የሚሻርበት መንገድ “የኪራይ ሰብሳቢነት” መንፈስ ይንፀባርቅበታል ” ሲል የተናገረው ደግሞ ፌዴራል ረዳት ዳኛ ማርቆስ ቱፋ ነው።\n– የአበበ ገላጋይን ምላሽ ከቆይታ በኋላ ይዘን እንቀርባለን።", "passage_id": "ffaa289f725a995d3afba611a49b9e37" }, { "passage": "የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አሰራሮችን እየተገበረ መሆኑን ገለፀ፡፡  ፍርድ ቤቱ በባለሙያዎች የተገልጋይ እርካታ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ የተገኙ ክፍተቶችና ጉድለቶችን በመለየት የተሻለ ለውጥና መሻሻል ለማምጣት እየሰራ መሆኑን የፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት የኔነህ ስመኝ ለዋልታ ገለፁ፡፡በጥናቱ ተገልጋዮች አሉ የሚሏቸውን ችግሮች ማስቀመጣቸውን ፕሬዚዳንቱ ጠቁመው በዚህ ዙሪያም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያየትና በመመካከር የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት እየተሰራ ነው፡፡የቀጠሮ ፖሊሲን ጠብቆ ያለመስራት አንዱ ችግር ሲሆን በዚህም ለፍርድ፣ምስክር ለመስማት፣ ለክርክር፣አጭርና ረጅም ጊዜ የሚወስዱ ጉዳዮችን በተመሳሳይ ሠዓት በመቅጠር ባለጉዳዮችን የማጉላላት አካሂድ በስፋት እንደሚስተዋል በጥናቱ ተመልክቷል፡፡የተዘዋዋሪና የፕላዝማ ችሎቶች በሙሉ አቅም አለመስራት፣ የቀጠሮ መርዘም፤አድሎአዊ አሰራርና ሙስና፣ ጠንካራ የመረጃ ማዕከል አለማደራጀት፣ ጠንካራ የፍርድ ቤት ውሳኔ አፈፃፀም አለመኖር፤ የፍርድ ቤቶችን አሰራር ለህብረተሰቡ በደንብ አለማሳወቅን የመሳሰሉ ችግሮች መኖራቸውም ተመልክቷል፡፡በጥናቱ የተለዩት ግኝቶች መኖራቸውን ያወሱት ፕሬዚዳንቱ ሁሉም ፍርድ ቤቶች የቀጠሮ ፖሊሲን መሰረት ያደረገ፣ እንደ ጉዳዮቹ ባህርይ ተገልጋዮችን በተለያየ ሠዓት በመቅጠር እንዲሰሩ ይደረጋል ብለዋል፡፡ሁሉም ተዘዋዋሪ ችሎቶች በሙሉ አቅም እንዲሰሩ፣አጭር ቀጠሮ በመስጠት ፍትሃዊ ሂደትን የተከተለ አሰራርን እንዲተገብሩ ይደረጋል፡፡ የፍርድ ውሳኔዎችም በፍጥነት እንዲፈፀሙ፣የመረጃ ማዕከልን በሰው ኃይልና በግብዓት የማደራጀት ሥራ እንደሚሰራም ነው የገለፁት፡፡በመብራት፣በኔትወርክና በቀላሉ ሊጠገኑ በሚችሉ የቴክኒክ ችግሮች ምክንያት የሚፈለገውን አገልግሎት መስጠት ያቆሙት የፕላዝማ ችሎቶች በሙሉ አቅም እንዲሰሩ የጀኔሬተር ግዥና የኔትወርክ መቆራረጥን ለማስቀረት ከሚመለከተው አካል ጋር ምክክር ተደርጓል ብለዋል፡፡ቀደም ሲል በክልል ደረጃ ስልሳ የፕላዝማ ችሎቶች አገልግሎት እየሰጡ ቢሆንም አሁን በትክክል አገልግሎት የሚሰጡት 15 የፕላዝማ ችሎቶች ብቻ ናቸው፡፡ ሌሎቹ በተለያዩ ምክንያቶች ከአገልግሎት ውጭ ሆነዋል፡፡ እነዚህ በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ እንዲገቡ ይደረጋል፡፡አፈፃፀማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ፍርድ ቤቶች ራሳቸውን በማሻሻል በጥናቱ ለተለዩት ድክመቶችና ጉድለቶች ዘላቂና አፋጣኝ መፍትሔ ይሰጣል፡፡ዳኞችና ሠራተኞች በህዝብ አገልጋይነት ስሜት እንዲሰሩ ማድረግ፣ አቤቱታ የሚቀርብበት ፎርም በማዘጋጀትና አገልግሎት አሰጣጡም በዜጎች ቻርተር መሰረት ይተገበራል፡፡ ይህን ጉዳይ የሚከታተል ፅህፈት ቤትም ይቋቋማል፡፡", "passage_id": "1733869ddac7289fcafdf434c2581f5a" } ]
3eb6c2a3f742c948c0876c0870ea65a9
ee203e37d248fe1f584b43566f3fb36d
ሁለተኛው የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሲ የምርጥ ቡና ቅምሻ ውድድር ይፋ ሆነ
ሰላማዊት ውቤአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ቡና ላኪዎችን ብቻ ሳይሆን አምራቾችን በስፋት ለማሳተፍ ያለመው ሁለተኛው የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሲ የምርጥ ቡና ቅምሻ ውድድር ይፋ ሆነ።ይሄን አስመልክቶም የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበሌ፣ የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር የሥራ አመራር ቦርድ ፕሬዚዳንት አቶ ደሳለኝ ጀና እና የውድድሩ አስተባባሪ ወይዘሪት ቅድስት ሙሉጌታ ትናንት በሄልተን ሆቴል በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ኃላፊዎቹ በሰጡት የጋራ መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ከፍተኛ ጥንቃቄ የተሞላበት ዓመታዊው ሁለተኛው የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሲ የምርጥ ቡና ቅምሻ ውድድር ከትናንት ጀምሮ ይፋ ሆኗል። በውድድሩ ናሙና ከአንድ የቡና ማሳ ይቀርባል። ከአንድ የቡና ማሳ በላይ በስሙ የተመዘገበ ማሳ ያለው አርሶ አደር ቢበዛ ሁለት ዓይነት ናሙና ማቅረብ ይችላል።ቡና ላኪዎችም የቡና ባለቤት አርሶ አደሮችን በመወከል ከአንድ በላይ ናሙና ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን፤ ነገር ግን የቡናውን ባለቤት አርሶ አደር ዝርዝር አድራሻ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። የቡና ማህበራት የቡና ማጠቢያ ጣቢያዎች ከአንድ በላይ ናሙና ማቅረብ ይችላሉ። የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ቡና ቅምሻ ውድድር በ2012 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣንና በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት በሚደገፈው “ፊውቸር ኢትዮጵያ ቫልዩ ቻይን አክቲቪቲ” ጋር በመተባበር መካሄዱን ያስታወሱት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበሌ፤ ለውድድር የሚቀርበው የናሙና ቡና መጠን ሦስት ኪሎ ግራም እንደሆነም ተናግረዋል።የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር የሥራ አመራር ቦርድ ፕሬዚዳንት አቶ ደሳለኝ ጀና በበኩላቸው እንደገለፁት፤የውድድሩ ሂደት ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ በሦስት ደረጃዎች የሚያልፍ ሲሆን፤ በብሄራዊ ባለሙያ ዳኞች፣ በዓለም አቀፍ የታወቁ የቡና ላቦራቶሪዎች ተገምግሞ ማለፍ የሚጠበቅበት መሆኑን አብራርተዋል።የዚህ ውድድር ያለፈው ዓመት የኢትዮጵያ አሸናፊ እ.ኤ.አ ጁላይ 24 ቀን 2020 በተካሄደ ጨረታ አንድ ኪሎ ግራም ቡና በ407 የአሜሪካ ዶላር መሸጡን የተናገሩት የውድድሩ አስተባባሪ ወይዘሪት ቅድስት ሙሉጌታ፤ ሂደቱ ይፋ የሆነበት መድረክ የጅማሮ ብስራት መሆኑንና በቀጣይ በተለያየ ጊዜ የሚደረጉ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛት ወርቁ በበኩላቸው፤ ውድድሩ እ.ኤ.አ በ1999 ብራዚል የተጀመረ መሆኑን እና ውድድሩ ለዓለም ገበያ የሚፈለገው ምርጥ ቡና ተወዳድሮ የሚወጣበት ዘዴ እንደሆነ ተናግረዋል። ዘዴው በተሻለ ዋጋ እንዲሸጥ ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር የተሻለ ቡና እንዲመረት የሚያበረታታ የማስታወቂያ ዘዴ ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ውድድር 1ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ማስገኘቱንና በዘንድሮው ዓመትም ከዚህ የበለጠ ይገኝበታል ተብሎ መታሰቡን ተናግረዋል።በመግለጫው ላይ የተገኙት የቡና ላኪዎች ማህበር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው አድማሱ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ለሁለተኛ ጊዜ የሚዘጋጀው የቡና ቅምሻ ውድድር ኢትዮጵያ በዓለም ቡና ገበያ ተገቢውን ዋጋ እንድታገኝ አመቺ ሁኔታዎችን ይፈጥራል። ውድድሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ቡና ላኪዎችን ብቻ ሳይሆን አምራቾችን በስፋት የሚያሳትፍና የሀገሪቱን የውጪ ምንዛሪ የሚያሳድግ ነው። በቡና የውጪ ንግድ ከተሰማሩት ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት በማህበሩ የታቀፉ ሲሆን፤ በማህበሩ ከተመዘገቡ 270 አባላት 245ቱ በዓለም ቡና ገበያ በከፍተኛ ደረጃ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37864
[ { "passage": " በመጭዎቹ የሰማንያ ዓመታት የጊዜ ጉዞ ውስጥ የኢትዮጵያ ቡና ከሚመረትበት አካባቢ ወደ ስድሣ ከመቶ የሚሆነው ክልል ለቡና ምርት የማይስማማ ሊሆን እንደሚችል ከትናንት በስተያ የወጣ አንድ የጥናት ሪፖርት አስጠንቅቋል፡፡ይህ ኔቸር ሪሰርች ወይም «የተፈጥሮ ምርምር» የሚባል ድርጅት በ«ኔቸር ፕላንትስ» ሕትመቱ ላይ ባወጣው ፅሁፍ በዓለም እጅግ ተወዳጅና ታዋቂም የሆነው «አራቢካ» እየተባለ የሚጠራው የኢትዮጵያ ውልድ የሆነ ቡና የሚያበቅለው አካባቢ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የመጎዳት ወይም የመጥፋት አደጋ ላይ መሆኑን አሳይቷል፡፡ጥናቱ የተካሄደው ለንደን የሚገኘው ኬው ሮያል ቦታኒካል ጋርደንስ ወይም የብዝኃ ዕፅዋት እንክብካቤና ምርምር ማዕከል ባልደረባ በሆኑት ዶ/ር አሮን ዴቪስና ጄስተን ሞት፤ እንዲሁም የኢትዮጵያው የተፈጥሮ አካባቢና የቡና ደን መድረክ ወይም በእንግሊዝኛ መጠሪያው ምኅፃር ‘ኢ.ሲ.ኤፍ.ኤፍ.’ ተብሎ በሚታወቀው ተቋም መሪ በዶ/ር ታደሰ ወልደማርያም ጎሌ ነው፡፡ወፍ ዘራሽ ሆኖ በተፈጥሮ የበቀለውና ዛሬ በዓለም ዙሪያ በስፋት እየተመረተም፤ እየተወደደም ያለው የቡና ዘር (በሣይንሳዊ መጠሪያው ‘ኮፊ አራቢካ’ ይባላል) የኢትዮጵያ ዝናባማ ጫካዎች የተፈጥሮ ሃብት - የእነርሱ ብቻ - መሆኑን ዶ/ር ታደሰ ወልደማርያም የዛሬ 14 ዓመት አውጥተውት የነበረ አንድ ፅሁፍ ይናገራል፡፡ ቡና 15 ሚሊየን ለሚሆን ኢትዮጵያዊ ገበሬ የለት ተለት ሕይወቱ የቆመበት ሃብት ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ደግሞ ከወጭ ንግድ ከምታገኘው ገቢ ሩብ ያህሉን የሚሸፍን ነው፡፡ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡ ", "passage_id": "574520686426c64d72948afcb282b3e9" }, { "passage": "–  በቻይና  ቤጂንግ  ከተማ  በሚገኘው  የስታር ባክስ ኬሪ  ማዕከል ለቡና መገኛዋ  ኢትዮጵያ  ክብር  የቡና ቀመሳ ሥነ ሥርዓት ባለፈው ማክሰኞ ተካሄደ።    በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ረዳት ኃላፊ አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ቡና በአይነቱ ለየት ያለ ጣዕም አለው። ስታርባክስ የኢትዮጵያን ቡና ለዓለም ለማስተዋወቅ ለሚያደርገው ጥረትም አምባሳደሩ ምስጋና ቸውን አቅርበዋል።ኢትዮጵያ በጣዕሙ ልዩ የሆነውን ቡና በማምረትና በከፊልም ምርቱን በማቀነባበር፤ ስታርባክስ ደግሞ ቡናው ለእያንዳንዱ ተጠቃሚ እንዲደርስ በማድረግ በኢትዮጵያና በስታርባክስ መካከል በተግባር የተገለጸ ትብብር መኖሩን አምባሳደሩ  ተናግረዋል።  በቻይና የስታር ባክስ ኩባንያ  የሕዝብ  ጉዳይ ምክትል ፕሬዘዳንት ዶንግዊ ሺ በበኩላቸው ስለ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ቡና ጣዕም መልካምነት በሥነ ሥርዓቱ ላይ ለታደሙት እንግዶች ማብራሪያ ሠጥተዋል ። ስታርባክስ ለዓለም ገበያ ከሚያቀርባቸው  የተፈጥሮ ቡናዎች  ልዩ  ጣዕም  ያላቸው  የሊሙና የሲዳሞ ቡና እንደሚገኙበት የአይጋ ፎረም ዘገባ ያመለክታል ።", "passage_id": "3c1f89b76081ba026def7433c4cec23a" }, { "passage": "አስቴር ኤልያስስፍራው ሞቃታማ ቢሆንም ቅጥር ጊቢው ግን በቡና ችግኞችና በተለያዩ የፍራፍሬ ዛፎች በመሙላቱ ለአይን አርንጓዴነቱ ደምቆ፤ ለአፍንጫ ደግሞ መልካም መዓዛው ዘልቆ ስለሚመጣ ለጎብኚው ማየትም መማግም ግዴታ ሳይሆን በውዴታ የሚያጣጥመው ነገር ነው። ወዲህ ለቡና ተክሉ የተስተካከለ ውሃ ይደርሰው ዘንድ አዲስ የሆነና የውሃው ልክ በኮምፒውተር የሚታዘዝበት ቴክኖሎጂ ያለበት አንድ ክፍል ይታያል፤ ወዲያ ደግሞ ወደ 750 ሜትር ኪዩብ ውሃ የሚይዝ የውሃው ሪዘርቫይር ይስተዋላል ፤ ቦታው በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ልዩ ስሙ ደበቃ እርሻ ልማት ነው። የቀርጫንሼ እርሻዎች አስተባባሪ ስራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ዳባ እንደሚሉት፤ በቀርንጫንሼ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ቀደም ሲል ጥራቱን የጠበቀ ቡና ወደ ውጭ አገር በመላክ ለአገሪቱ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ረገድ በግንባር ቀደምትነት እየሰራ ነው። ከንግዱ በተጨማሪ ከቅርብ ጊዜ ወደዚህ ጎን ለጎን በቡና እርሻ ልማት ተሰማርቷል። ድርጅቱ፣ በዓለማችን ላይ ዘመናዊ የሆነ በቡና ማምረት ቴክኖሎጂ ጫፍ ከደረሱ እንደብራዚል ካሉት አገራት ባልተናነሰ ዘመናዊ ቴክሎጂን ወይም ዲሪፕ እሪጌሽንን በመጠቀም ወደቡና ልማት እርሻ የገባ ነው። የቡና እርሻው የሚገኘው በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ልዩ ስሙ ደበቃ እርሻ ልማት ሲሆን፣ያረፈው ደግሞ በ72 ሄክታር መሬት ላይ ነው። በዚህም ላይ 110 ሺህ የቡና ችግኞችን በመተክል ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይም በአንድ ሄክታር ላይ ዘመናዊ የቡና ማፍያ የችግኝ ጣቢያ ወይም ዲጂታል ስፕሪንግ ክለር እሪጌሽ በመጠቀም 600 ሺህ ችግኞችን በማፍላት ለአካባቢው ህብረተሰብም ጭምር ለማደል ወደ ስራ መግባታቸውን ይናገራሉ። ቀደም ሲል በአገራችን ያለው አስተሳሰብ ቡናን ያለጥላ ዛፍ ማልማት አይቻልም የሚል ኋላ ቀር አስተሳሰብ ሲሆን፣ ይህን አስተሳሰብ በአዲስ አስተሳሰብ ለመቀየር እየሰራን ነው ሲሉ ያስረዳሉ። በድርጅቱ አግሮኖሚስት ሆነው የሚሰሩት የሆርቲካልቸር ባለሙያው አቶ ጉተማ ጎቤ በበኩላቸው፤ በድሪፕ እሪጌሽን (ጠብታ መስኖ) በአንድ አይነት መልኩ ውሃ ለቡናው እንዴት ሆኖ ይሰራጫል የሚለውን እንደሚከታተሉ ይናገራሉ። ውሃው ለችግኙ ሲደርሰው ለእያዳንዱ ቡና እኩል የሆነ የውሃ መጠን ነው በሜትር ኪዩብ የተለቀቀው ውሃ ወደ ቡናው ሲሄድ የሚደርሰው በሚሊ ሊትር ተቀይሮ መሆኑን ይጠቅሳሉ። ይህ ቴክኖሎጂ የነበረውን ተልምዷዊ አሰራር ያለዛፍ ቡና መብቀል አይችልም የሚል አስተሳሰብን የሰበረ ነው። ቀደም ሲል ዛፍ ያስፈልግ የነበረው ብዙ ውሃ ስለማይጠጣ የዛፍ ጥላው ያለውን ውሃ እርጥበቱን ጠብቆ እንዲሄድ ስለሚያርገው ነው ይላሉ። አጠቃላይ የቀርጫንሼ ካምፓኒ ስራ አስፈጻሚ አቶ እስራኤል ደገፋ፣ ካምፓኒው የሚሰራው አጠቃላይ የአገራችን ኢኮኖሚ በሚፈልግበት በግብርናና ማኑፋክቸሪንግ ላይ መሆኑን ይገልጻሉ። በግብርናው ላይ ወደ 26 ሺህ የስራ እድሎችን በመፍጠር እንዲሁም ከ56 ሺህ አርሶ አደሮች ጋር የገበያ ትስስር በመፍጠር የሚሰራ ድርጅት እንደሆነም ያመለክታሉ። አቶ እስራኤል እንደሚሉት፤ ላለፉት አራት አምስት ዓመታት ትልቁን የአገሪቱን የቡና ኤክስፖርት ከሁለት አኃዝ በላይ ድርሻ በመውሰድ የሚልከው ይኸው የቀርጫንሼ ኩባንያ ነው። በየትኛውም የኢትዮጵያ ቡና አብቃይ ክልሎችም ሆነ ወረዳዎች ይገኛል። አጠቃላይ ወደ 57 ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ደግሞ ወደ አምስት እርሻዎችን በቡናው ሴክተር ላይ ማኔጅ ያደርጋል። ጉብኝት የተደረገበት የደበቃ እርሻ ጣቢያ፣ ኩባንያው ካሉት እርሻዎች ሁሉ አነስተኛው ነው ያሉት አቶ እስራኤል፣ ነገር ግን እንዴት አድርገን ግብርናን\nከተለምዶ አሰራራችን መቀየር አለብን ሲሉ በማሰብ በቡናው ፋርም ትልቅ ደረጃ ላይ የደረሱ አገሮችን\nተሞክሮ ከእነእስራኤልና ብራዚል መውሰድ ላይ መሆናቸውን ያመለክታሉ።\nየወሰዱትም ቴክኖሎጂ ድሪፕ ኢሪጌሽን ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት በዓለም ላይ የመጨረሻው የሚባለው\nበግብርናው ዘርፍ የተገኘና\nውጤታማ የሆነ የመስኖ ሲስተም ነው ይላሉ። ከዚህ አንጻር በደበቃ ያለው የተሻለው\nቴክኖሎጂ  እንደሚያሰኘው ያስረዳሉ።\nአርሶአደሩ በተለምዶ በሄክታር ቡና የሚያገኘው ከስድስት ኩንታል የዘለለ አይደለም የሚሉት አቶ እስራኤል፣ እኛ በዚህ ቴክኖሎጂ ተጠቅመን ግን በሄክታር እስከ 35 ኩንታል ማሳካት ችለናል ብለዋል። ይህ ሙከራ ደግሞ የመጀመሪያው ሲሆን፣ የሚጠበቀው በሄክታር እስከ 65 ኩንታል ድረስ ነው ብለን እየሰራን ነው ሲሉ ተናግረዋል። ያንን ማሳካት ከቻልን የአገራችንን የውጭ ምንዛሬ ማሳደግ እንዲሁም የአርሶ አደሮችን ገቢ ከፍ ማድረግ ይቻላል ብለዋል። የእኛ ትልቁ እቅዳችን የራሳችን ማሳ ላይ ትልቁን ምርት ማምረት ላይ ብቻ አይደለም። በአቅራቢያው የሚገኙ የአርሶ አደሮችንም ማሳዎች ወደእኛ ቴክኖሎጂ በመቀየር እነርሱም ተጠቃሚ የሚሆኑበትን መሰረት ማደላደልና በፋይናንስም ለመደጎም ሲሆን፣ ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ዲዛይን አድርገን ጨርሰናል ይላሉ። በዕለቱ ቀርጫንሼ ትሬዲግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ኤክስፖርት ስታንዳርድ የቡና ላቦራቶሪን የመረቁት የግብርና ግብአትና ግብይት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ እና የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ ሲሆኑ፣ ሚኒስትር ዴኤታዋ በዕለቱ እንደተናገሩት፤ የድርጅቱን የቡና ማዘጋጃ መጋዘንና የቡና መቅመሻ ላቦራቶሪ እንዲሁም እርሻዎቹን ጎብኝተናል። ከዚህ ደርጅት ባለቤት ጋር አርሶ አደሮችም አብረው ነው ያሉት። ለምርት መሻሻል ደግሞ ዋናው አርሶ አደሮቻችን ከባህላዊ የቡና አመራረት ዘዴ በመጠኑም ቢሆን በመቀየር የቡናን ምርታማነት ሊቀየሩ የሚችሉ አሰራሮችን ተግባራ እያደረጉ ነው ያሉት። ቡሌ ሆራ ላይ እንደማየውና ሞዴል አርሶአደሮችም እንዳረጋገጡልን በምርትም፣በአቅርቦትም ሆነ በገበያ ትስሰርም የተሻለ እድል ያለበት አካባቢ መሆኑን ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፣ እዚህ የሚሰሩ ባለሀብቶች የአርሶአደሩንም ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ስለመሆናቸው ማስተዋል መቻላቸውን ይናገራሉ። እርሳቸው እንደሚናገሩት፤ እንደግብርና ሚኒስቴር የበለጠ ምርትና ምርታማነትን ሊያሳድግ የሚችል ስራ ይሰራሉ። ቡና ወደውጭ በመላክ ረገድ በተለይ ቀርጫንሼ ላለፉት ሁለትና ሶስት ዓመታት የቀዳሚነት ድርሻውን እየተወጣ ነው። በመጋዘን ውስጥ የተመለከትነውም ደረጃውን የማያስለቅቅ ለአገርም ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያደርግ የሚችል ክምችት የያዘ ቡና መኖሩን ነው፤ ለዚህም በጣም ደስተኞች ነን። አርሶአደሮቹ ጥሩ የቴክኖሎጂ ስራ ካላቸው ከግል ሴአልሚዎች ጋር በመቀናጀት ምርታቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ የሚያስችል የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ነው። የተሻለ ገበያ እንዲያገኝ ከማድረግ አኳያ የተዘረጉ አሰራሮች አሉ፤ ትልቁ ነገር አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርት ቀጥታ ወደ ገበያ ለማድረስ የሚያስችለው አቅም ገበያ የማፈላለግ ችሎታ የማዳበር ስራ መሰራት ይኖርበታል። እንዲህ ከሆነ በለፋው ልክ ጥቅም እንዲያገኝ ያችለዋልና በዚህ ደረጃ እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል ብለዋል። ዶክተር አዱኛ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ባለስልጣኑ ቡና ከማብቀል ጀምሮ ውጭ አገር እስከ መላክ ድረስ ያለውን ሂደት በማገዝ እንዲሁም ገበያ በማፈላለግ ረገድ በመስራት ላይ ይገኛል። አርሶ አደሮቻችን እስከ ውጭ አገር በራሳቸው እንዲልኩ ይሰራል። 500 ያህል አርሶ አደሮች ወደውጭ አገር መላክ የሚያስችላቸውን ሰነድ አውጥተዋል። በዚህም እየሄዱበት ነው። ቀርጫንሼ የሰራው ስራ በአርአያነት መጠቀስ የሚያስችል ስራ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ በቦታው ተገኝተን ያስተዋልነው ነገር ቢኖር ይህን ነው ብለዋል። ይህም ወደሌሎቹም መስፋፋት ያለበት ቴክኖሎጂ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ስራው ደግሞ እንደ መንግስት ድጋፍ እናደርግለታለን ብለዋል።አዲስ ዘመን ጥር 10/2013 ዓ.ም ", "passage_id": "f9449b088f1a08d6bf35cd59620085c8" }, { "passage": "ከዚህ ቀደም በቡና አምራችነታቸው የማይታወቁት የትግራይና የአማራ ክልሎች ቡና ማምረት የሚያስችላቸው አዲስ ዕቅድ ተዘጋጀ፡፡በከፍተኛ ደረጃ በቡና ምርት የሚታወቁት ደቡብና ኦሮሚያ ክልሎች ናቸው፡፡ በአነስተኛ ደረጃ በቡና ምርት የሚታወቁት ደግሞ ጋምቤላና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ናቸው፡፡ ትግራይና አማራ ከቡና ምርቶች ጋር ስማቸው ተያይዞ አያውቅም፡፡ ነገር ግን የእርሻና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር አዲስ በነደፈው ዕቅድ፣ የቡና ምርት መልክዓ ምድራዊ ካርታ ከደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍል፣ ወደ ሰሜናዊው የአገሪቱ ክፍል እንዲለጠጥ አድርጓል፡፡በዚህ መሠረት በትግራይ ክልል ደቡብ ትግራይ ዞን ራያ፣ አላማጣና መሆኒ፣ በአማራ ክልል ደግሞ ምዕራብ ጎጃም፣ ሰሜን ሸዋ፣ ደቡብ ወሎ፣ አዊ እና ጎንደር የተለያዩ የተመረጡ ወረዳዎች ቡና ለውጭ ገበያ እንዲያቀርቡ ታጭተዋል፡፡የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር የቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍቅሩ አመኑ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች ቡና ማምረት ከተጀመረ ረዥም ጊዜ እንደመሆኑ አመራረቱ ባህላዊ ነው፡፡ በአንፃሩ አማራና ትግራይ ክልሎች ለቡና ምርት አዲስ በመሆናቸው በዘመናዊ መንገድ ቡና ማምረት የሚያስችላቸው ዝግጅት ተደርጓል፡፡ በአሁኑ ወቅት ገበሬዎች በመከራ ቡና እያመረቱ ናቸው፡፡‹‹በሙከራ ደረጃ የትግራይ ቡና ከሐረር ስፔሻሊቲ ቡና ጋር ተመሳሳይነት አለው፤›› ያሉት አቶ ፍቅሩ፣ ‹‹በአማራ ክልልም እንዲሁ ተወዳጅ ጣዕም ያለው ቡና የሚመረት በመሆኑ፣ ምርቱን በዘመናዊ መንገድ ለማልማት ታቅዷል፤›› ብለዋል፡፡በትግራይና በአማራ በዘመናዊ መልክ የሚመረቱ ቡናዎች ከሌሎች አካባቢዎች የተለየ ጣዕም ያላቸው በመሆኑ ሳይቀላቀሉ ለገበያ የሚቀርቡበት አሠራር ከመፍጠር በተጨማሪ፣ በዓለም ገበያ ውስጥ ተመራጭ እየሆነ የመጣው ከማሳ ጀምሮ የሚታወቅ የአመራረት ሥልት ተግባራዊ እንደሚደረግ አቶ ፍቅሩ አስረድተዋል፡፡ወደ እነዚህ አካባቢዎች የቡና ምርትን ማስፋት ሁለት ጠቀሜታዎች እንዳሉትም አቶ ፍቅሩ ገልጸዋል፡፡ የመጀመሪያው አገሪቱ ከቡና የውጭ ገበያ የምታገኘውን ምንዛሪ ማሳደግ ነው፡፡ ሁለተኛው ድርቅ በሚያጠቃቸው አካባቢዎች ቋሚ ሰብል ቢኖር፣ አርሶ አደሮችም ሆኑ አርብቶ አደሮች በቋሚ ሰብሎቹ ድርቅ የሚያሳድርባቸውን ጉዳት እንዲቋቋሙ የሚያስችል መሆኑ ነው፡፡በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን አርሶ አደሮች በቡና ምርት ይተዳደራሉ፡፡ እነዚህ አርሶ አደሮች በሥራቸው አምስት ቤተሰብ አለ ቢባል በዘርፉ 25 ሚሊዮን ሕዝብ ይተዳደራል፡፡ ዘርፉ የፈጠረው የሥራ ዕድልና ሀብት ከፍተኛ እንደሆነም ይነገራል፡፡ የቡና ምርቱ አምስት ሚሊዮን ሔክታር መሬት ይሸፍናል፡፡ባለፈው የበጀት ዓመት በሚኒስቴሩ ጥናት መሠረት 548 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ቡና ተመርቷል፡፡ ይህንን ምርት በዚህ ዓመት ከእጥፍ በላይ የመጨመር ዕቅድ ተይዟል፡፡ባለፈው በጀት ዓመት ከተመረተው ምርት 256,775 ሜትሪክ ቶን ቡና ለኢትዮጵያ ምርት ገበያ የቀረበ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 183 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ቡና ለውጭ ገበያ ተልኳል፡፡በቡና ላይ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ኅዳር 15 ቀን 2008 ዓ.ም. የሚኒስትሮች ምክር ቤት እንዲቋቋም የወሰነው አዲሱ የቡናና  ሻይ ግብይት ባለሥልጣን ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ ይህንን ባለሥልጣን የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር በማደራጀት ላይ ይገኛል፡፡በፌደራል ደረጃ ከሚደራጀው ከዚህ ባለሥልጣን በተጨማሪ፣ ኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች ተመሳሳይ መሥሪያ ቤት እንዲያደራጁ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉል፣ ትግራይና አማራ ክልሎች ባለሥልጣን ባይሆንም፣ ምርቱን የሚቆጣጠርና የሚያስፋፋ ክፍል እንዲያዋቅሩ መግባባት ላይ መደረሱን አቶ ፍቅሩ ገልጸዋል፡፡በፌደራል ደረጃ የሚቋቋመው የቡናና ሻይ ባለሥልጣን ከንግድ ሚኒስቴር የቡና ግብይት ክፍልና ከእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር ደግሞ የቡና ሻይና ዳይሬክቶሬት ይዞ በአዲስ መልክ የሚደራጅ መሆኑ ታውቋል፡፡ ባለሥልጣኑን የሚመራው ዋና ዳይሬክተር በቅርቡ ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡", "passage_id": "45f71b2ca8a9ed4921d3cea403be974a" }, { "passage": "የአውሮፓ ሕብረቱ ካፌ ፕሮጄክት የኢትዮጵያን የቡና ምርት ለማሳደግ የሚያስችል የ15 ሚሊየን ዩሮ ፕሮጄክት ይፋ ማድረጉን አስታወቀ፡፡የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሳኒ ረዲ ፕሮጄክቱ ይፋ በተደረገበት ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከዘርፉ የሚገኘው ጥቅም ከምርቱ አንፃር ዝቅተኛ በመሆኑ ፕሮጄክቱ ይህን ችግር በመቅረፍ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡\nየካፌ ፕሮጄክት አስተባባሪ አቶ ፍቅሩ አመኑ በበኩላቸው ፕሮጄክቱ በቡና ምርት ላይ የሚደረገውን የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል፡፡ፕሮጄክቱ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ ሲሆን በአማራ፣ ደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም ኦሮሚያ ክልሎች በሚገኙ 28 ቡና አምራች ወረዳዎች ተግባራዊ ይሆናል፡፡", "passage_id": "9d4426f36950f5ba15a78082eebc5856" } ]
de4c9d9d2ae3c0b46f55f0b29057738e
097a510b2f5bdaf32d9d5ecc7f0cac2c
የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በአዲግራት ከተማ የደረሰውን ጉዳት ጎበኙ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ እና የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በአዲግራት ከተማ የህወሓት ጁንታ ያደረሰውን ጉዳት ጎብኝተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአዲግራት ከተማ ሰላም እየተመለሰ እንደሆነም ተነግሯል፡፡ኢዜአ እንደዘገበው፤ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ እና በትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ዶክተር አብርሃም በላይ የተመራ ልዑክ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲና በአዲስ መድሃኒት ፋብሪካ ላይ የደረሰውን ውድመት ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡በጉብኝቱም የህወሓት ጁንታ ለህዝብ የማያስብ እና ከህዝብ አብራክ የወጣ የማይመስል የጥፋት ቡድን መሆኑን በመሰረተ ልማቶች ላይ ባደረሰው ጥፋት ማሳየቱ በግልጽ እንደታየ የተገለጸ ሲሆን፤ የህወሓት ጁንታ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ዝርፊያ ከመፈጸም አልፎ የቀረው ንብረት ለመጪው ትውልድ እንዳያገለግል ሰባብሮ እና ከጥቅም ውጪ አድርጎ መፈርጠጡም ተነግሯል።በአዲግራት ከተማ በሚገኘው አዲስ መድሃኒት ፋብሪካም ተመሳሳይ ድርጊት የፈጸመ ሲሆን፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዶክተር ሙሉ ነጋ ቡድኑ በህዝብና በመንግስት ንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱን ጠቁመዋል፡፡ የቡድኑ የህገወጥ ድርጊት ሰለባ የነበረችው የአዲግራት ከተማ ሰላም በአሁኑ ወቅት እየተመለሰ እንደሆነም ተናግረዋል።በቀጣይ በትግራይ ክልል አጠቃላይ በህወሓት ጁንታ የደረሱ ጉዳቶች ተጠንተው ለፌዴራል መንግስት ቀርበው መፍትሄ እንዲያገኙ የሚደረግ ስለመሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፤ የጉብኝት ልዑኩ የአካባቢውን ሰላም ለመጠበቅና የፈረሰውን የመንግስት መዋቅር መልሶ ለማቋቋም ከአዲግራት ከተማ ወጣቶች ጋር ምክክር አድርገዋል፡፡ በምክክር መድረኩ በጋራ ለመስራት የሚያስችል መግባባት ላይ ተደርሷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37855
[ { "passage": "የመከላከያ ሰራዊትና አማራ ልዩ ኃይል በተቆጣጠሯቸው የራያ አላማጣ አካባቢዎች አንጻራዊ ሰላም መስፈኑን አካባቢውን የማየት እድል ያጋጠማቸው ግለሰቦች ገለጹ፡፡መከላከያ ሰራዊት ሰብአዊ ጉዳት እንዳይደርስ ላደረገው ጥንቃቄ ምስጋናቸውን ገልጸዋል አስተያየት ሰጭዎች፡፡የፌዴራሉ መከላከያ ሰራዊት ከአማራ ልዩ ኃይል ጋር በመሆን በወሰደው ወታደራዊ ጥቃት ከተቆጣጠሯቸው ቦታዎች ዋጃ፣ ጥሙጋ፣ አለማጣና በአላማጣ ዙሪያ ያሉ አካባቢዎች እንደሚገኙበት የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን በዘገባቸው አስታውቀዋል፡፡\n", "passage_id": "a7fd1ac13191455f4a93d31fbb0f9b9b" }, { "passage": "መቀለ ከተማ\n\nበትግራይ ክልል መቀለ ከተማ ትናንት ግንቦት 21 ቀን 2012 ዓ.ም ጠዋት አንዲት ሴት ከታጣቂ ሚሊሻ በተተኮሰ ጥይት መገደሏን የመቀለ ከተማ ወንጀል መከላከልና ምርመራ ፅ/ቤት ለቢቢሲ ገልጿል።\n\nከፖሊስ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው በስም ያልተጠቀሱት ግለሰቦቹ በሥራ ክፍያ ሳይስማሙ ቀርተው አለመግባባታቸው ተባብሶ ታጣቂው ተኩሶ ገድሏታል።\n\nታጣቂው በተኮሰባት ጥይት የተመታቸው ሴት፤ ህይወቷ ወዲያውኑ አልፏል ብሏል ፖሊስ። ታጣቂው ግድያውን ከፈፀመ በኋላ ራሱ ላይ በመተኮሱ ለጉዳት ተዳርጎ ወደ አይደር ሪፈራል ሆስፒታል መወሰዱን እና በሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና ተደርጎለት በፖሊስ ጥበቃ ሥር ሆኖ ህክምና እየተከታተለ እንደሚገኝ ፅ/ቤቱ አስታውቋል።\n\n ", "passage_id": "36a7a0db7d3e0bfc6091c1202b95678a" }, { "passage": "የመከላከያ ኃይል ስምሪት መምሪያ ሃላፊ ብርጋዴል ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው በጉዳዩ ላይ ለኢዜአ መግለጫ ሰጥተዋል።በመግለጫቸው በርካታ የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችና ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውንና መደምሰሳቸውን ገልፀዋል።ብርጋዴል ጄኔራሉ የመከላከያ ሃይልና የፌዴራል ፓሊስ በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ በርካቶች መማረካቸውንና እጅ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑት መደምሰሳቸውን አስታውቀዋል።የተደበቁትን የቡድኑን አባላትን እግር በእግር እየተከታተሉና እየፈተሹ መሆኑን ገልፀው ፍለጋው ከሰፊ ወደ ጠባብ መጥቷል ብለዋል።እየተካሄደ ባለው ፍተሻ የቡድኑ አመራሮች በየዋሻውና በየቤተክርስቲያኑ ተደብቀው መገኘታቸውንና የቤተክርስቲያን አባቶችን አልባሳት ለብሰው የተገኙ መኖራቸውን ተናግረዋል።ብርጋዴል ጄኔራል ተስፋዬ ከመከላከያ ሠራዊት ከድተው ቡድኑን በተቀላቀሉና እጅ ስጡ ሲባሉ አንሰጥም ባሉ አመራሮች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል።በዚሁ መሰረት የማይካድራውን ጭፍጨፋ የመራው ኮሌኔል የማነ ገብረሚካኤልን ጨምሮ እርምጃ የተወሰደባቸውን የህወሓት ቡድን አመራሮች ዝርዝር ይፋ አድርገዋል።እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል ኮሎኔል አለም ገብረመድህን፣ ኮሎኔል ቢንያም ገብረመድህን፣ ኮሎኔል አምባዬ፣ ኮሎኔል ማሾ፣ ኮሎኔል ይርጋ ስዩም፣ ኮሎኔል ሃዱሽ፣ ኮሎኔል አጽብሃ፣ ኮሎኔል ተስፋዬ ገብረመድህን፣ ኮሎኔል ዮሃንስ ካልአዩ፣ ኮሎኔል ተክለእግዚአብሄር፣ ሌተናል ኮሎኔል ብርሃኔ ቶላ እና ሌሎች በስም ያልተገለጹ አራት ኮሎኔሎችና ሁለት የዞን አመራሮች ይገኙበታል።እጅ ከሰጡ የጁንታው አመራሮች መካከልም የቀድሞ የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሙሉ ገብረእግዚአብሔር እንደሚገኙበት አክለዋል።በተመሳሳይ ሃዱሽ ዘውገ ገዛኸኝ የክልሉ ኦዲት ሀላፊ የነበረ፣ ሰለሞን ህሉፍ ንጉሴ የክልሉ ልማት ስልጠና ሀላፊ የነበረ፣ ኪዳነማሪያም ገብረክርስቶስ ፋሲል የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ የነበረ፣ ባህታ ወልደሚካኤል የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ የነበረ፣ ሀጎስ ወልደኪዳን ገብረማሪያም የክልሉ ኢኮኖሚ ቢሮ የልማት እቅድ አስተባባሪ እጅ መስጠታቸውን ገልፀዋል።በተጨማሪም በርካታ ቁጥር ያላቸው የሚሊሻና ልዩ ሀይል አባላት እጃቸውን መስጠታቸውን ነው የተናገሩት።ከተማረኩ የህወሓት አባላት ዶክተር ዓለም ብርሃኔ፣ ኮሎኔል መብርሃቱ ገብረመድን፣ ኮሎኔል ሃዱሽ ሃጎስ፣ ኮሎኔል ህሉፍ ተ/መድህን፣ ሌተናል ኮሎኔል ተክለ ህይወት አሰፋ ይገኙበታል ብለዋል ብርጋዴል ጄኔራሉ።ለጥፋት ሲቀሰቅስ የነበረ የህወሓት ቡድን አባል ገብረአምላክ ይኸብዮ የተባለ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ምሁር መማረኩንም ገልፀዋል።የተደበቁ የህወሓት አመራሮች ከማንም ጋር የሚገናኙበት ዕድል እንደሌላቸው ገልጸው፤ በየቤተክርስቲያንና በየዋሻው ራሳቸውን ቀይረው ሲንቀሳቀሱ እየተያዙ መሆኑን ገልጸዋል።የጥፋት ቡድኑ የራሱ አመራሮች ሲሞቱ በሰውነታቸው ላይ የፈፀመውን ጭካኔ የተሞላበት ደርጊትም ገልፀዋል።የመከላከያ ሠራዊት የህወሓት \"ሽማግሌ አመራሮችን\" ይዞ በቅርቡ ዜናው ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንደሚደርስ ተናግረዋል።", "passage_id": "0ce6e483f426437a19298e854a2a430f" }, { "passage": "በትግራይ ክልል መቀለ ከተማ በርካታ የክልሉ የልዩ ኃይል አባላትና ታጣቂ ሚሊሻዎች በዛሬው ዕለት ወታደራዊ ሰልፍ በማካሄድ ትዕይንት አድርገዋል።በሰልፉ ላይ የተሳፉት የልዩ ኃይልና የሚሊሻ አባላቱ ቀላልና ከባድ የጦር መሳርያዎችን ታጥቀው መታየታቸውን የቢበሲ ዘጋቢ ከመቀለ ገልጿል። ዛሬ ረፋድ ላይ በክልሉ ዋና ከተማ በመቀለ ጎዳናዎች ላይ በሰልፍ ሲጓዙ የታዩት ወታደራዊ የደንብ ልብስ የለበሱት የልዩ ኃይሉ አባላትና ሚሊሻዎች በከተማው ወደሚገኘው ስታድየም በመጓዝ ተሰብስበው ታይተዋል።በመቀለ ከተደረገው ከዚህ ወታደራዊ የሰልፍ ትዕይንት ባሻገር በሌሎችም የክልሉ ከተሞች ጭምር መደረጉ ለማወቅ ተችሏል።ቢሆንም ይህ ዛሬ የተካሄደው ወታደራዊ ሰልፍ ዓላማው ምን እንደሆነ የትግራይ ክልል መንግሥት የገለጸው ነገር የለም። ነገር ግን የትግራይ ክልል የጸጥታ ቢሮ ፌስቡክ ገጹ ላይ \"ለሰላም ሲባል ለሚከፈል ዋጋ ሁሌም ዝግጁ ነን\" የሚል መልዕክት አስፍሯል። ቢሮው አክሎም \"የአንድ ሕዝብ የሰላሙ ዋስትና ውስጣዊ አቅሙ እንጂ የማንም የውጭ ኃይል ድጋፍና ጥበቃ ሆኖ አያውቅም\" ሲል ገልጿል። የእዚህ ወታደራዊ ትዕይንት ዓላማ ባይገለጽም የትግራይ ክልል መንግሥት ከፌደራሉ መንግሥት በኩል ይደርስብኛል የሚለውን ጫና ለመመከት እየሰራ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል።የቀድሞው ገዢ ፓርቲ ኢህአዴግ ከከሰመና የትግራይ ክልል ገዢ ፓርቲ ህወሓት ከአዲሱ የብልጽግና ፓርቲ እራሱን ካገለለ በኋላ በፌደራሉ መንግሥትና በትግራይ ክልል መካከል ያለው አለመግባባት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተካረረ መጥቷል። ይህም ሁኔታ በሁለቱ ወገኖች መካከል የኃይል ግጭት ሊከሰት ይችላል የሚል ስጋት ከአንዳንድ ወገኖች በኩል ሲነሳ ቆይቷል። ባለፈው ሳምንት ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር በተደረገ ውይይት ላይ የፌደራል መንግሥት ከትግራይ ክልል ጋር ምንም አይነት ፍጥጫ ውስጥ የመግባት ፍላጎት እንደሌለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ተናግረዋል።በዚህም \"ማን ነው ማንን የሚወጋው? ለምንድነው የፌደራል መንግሥት ትግራይን የሚወጋው? ይህ የእብደት ንግግር ነው። የፌደራሉ መንግሥት የራሱን ሕዝብ የመውጋት ሃሳብና ፍላጎት ፍጹም የለውም\" ብለው ነበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ።ነግ ግን የትግራይ ክልል መንግሥት ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተያየት እውነታውን አያንጸባርቅም ሲል አጣጥሎታል።የትግራይ ክልል መንግሥት ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫም \"ስልጣን ላይ ያለው አሃዳዊ አምባገነን ቡድን የትግራይ ሕዝብና መንግሥት ምርጫ አካሂዳለሁ በማለቱ ብቻ 'ተዘጋጅቻለሁ፣ እናቶች ያለቅሳሉ፣ የወጣቶች ደም ይፈስሳል፣ መሰረተ ልማት ይወድማል' ሲል በአደባባይ ፎክሯል\" ሲል የፌደራል መንግሥቱን ከሷል።ባለፉት ሁለት ዓመታት በትግራይ ክልልና በፌደራል መንግሥቱ መካከል ያለው አለመግባባት ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰው ለነሐሴ ወር የተያዘው አጠቃላይ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወርሽኝ ሰበብ መራዘሙን ተከትሎ ነው።የምርጫውን መራዘም የትግራይ ክልል የተቃወመው ሲሆን ከሌሎቹ የአገሪቱ ክልሎች ተለይቶ በተናጠል ምርጫውን ለማካሄድ ወስኖ አስፈላጊ የተባሉትን ሥራዎች እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል።በዚህም ሳቢያ ባለፈው ሳምንትም የፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል ምርጫ ለማካሄድ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በአፋጣኝ እንዲያቆም የሚጠይቅ ደብዳቤ ፅፏል። በደብዳቤው ላይ ክልሉ በዚህ ውሳኔው የሚገፋ ከሆነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት \"በሕገ መንግሥቱና ሌሎች ሕጎች የተሰጠውን ስልጣን ለመተግበር እንደሚገደድ\" ማስጠንቀቁ ይታወሳል። ", "passage_id": "012a8c586581e13a1af65cac08927e8c" }, { "passage": "ለሀገር ህልውና፣ ሰላምና ልማት በጋራ መቆም እንደሚያስፈልግ የመቐለ ከተማ የሃገር ሽማግሌዎች አስገነዘቡ።የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በክልሉ የተለያዩ ከተሞች በመዘዋወር ህዝብ በማወያየት ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ በመቐለ ከተማም ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።በመቐለ ከተማ ከጊዜያዊ አስተዳዳሩ ጋር ውይይት ያደረጉት የሀገር ሽማግሌዎች ለሃገር ህልውና፣ ሰላምና ልማት በጋራ መቆም እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።“ያለችን አንዲት ሀገር ነች፣ ሰላማችንን እውን ማድረግ የምንችለውም እኛው ነን፤ በአንድ ሃገር ላይ ሁለት የተለያየ የታጠቀ አካል ካለ ደግሞ ችግር ያስከትላል” ብለዋል።በመሆኑም በህወሓት የጥፋት ቡድን በህገ ወጥ መንገድ የታጠቁ የመቐለ ወጣቶች መሳሪያቸውን በሰላማዊ መንገድ ለመከላከያ ሠራዊት እንዲያስረክቡ የሃገር ሽመግሌዎች ጠይቀዋል።የህወሓት ቡድን በጫና በርካታ ወጣቶችን በማስታጠቅ በተለይ በክልሉ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር መስራቱ ተቀባይነት የሌለው መሆኑንም ገልጸዋል።የሀገር ሽማግሌዎቹ የትግራይ ህዝብ የሚፈልገው ሰላም፣ ልማትና አብሮነትን እንደሆነ ገልጸው፤ የህወሓት ቡድን ወጣቶችን በማስታጠቅ ወደ ግጭትና አለመረጋጋት ማምራቱን አውግዘዋል።በህገ ወጥ አካል መሳሪያ የታጠቁ ወጣቶች መሳሪያውን በአፋጣኝ ለመንግስት ገቢ እንዲያደርጉ መጠየቃቸውንም ኢዜአ ዘግቧል።", "passage_id": "2e8fe494f3b4643bd07377fd4d98c889" } ]
b8d882a01aff078db2ac894299296f37
25f7a25047223f2c685c3d9b5d8f1f6d
ሙስናን በዘላቂነት ለመከላከል ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በሀገሪቱ የሚስተዋለውን ሙስናን በዘላቂነት ለመከላከል ህዝቡን በአግባቡ በማሳተፍ መስራት እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ አቶ ታገሠ ጫፎ ገለጹ።ሀገር አቀፍ የፀረ- ሙስና መድረክ ትናንት በጎንደር ከተማ ተጀምሯል።እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ አፈጉባኤው ሙስናን መታገል በዋናነት ከራስ እንደሚጀመር አመልክተው፤ የሀገሪቱን እድገት የሚፈታተን በመሆኑ ጊዜ ሳይሰጠው ህዝቡን በአግባቡ ማሳተፍ፣ በተደራጀ አግባብ መከላከልና ማስቆም እንደሚገባ አሳስበዋል። በሀገሪቱ ሙስናን ለመታገል የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስፈላጊውን እገዛ ያደርጋል ያሉት አፈ ጉባኤው፤ ሙስና በሀገሪቱ የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ እንዳያስተጓጉል በፅናት መታገል እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት።በመድረኩ የፌዴራል የሥነ- ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ፀጋ አራጌና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘው ተሻገርን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።ለሁለት ቀናት በሚካሄደው በዚህ መድረክ በፀረ ሙስና ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፎች እንደሚቀርቡና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ታውቋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37865
[ { "passage": "ህብረተሰቡ በመንግሥት የተጀመረውን የጸረ-ኪራይ ሰብሳቢነት ትግል በመቀላቀልና በባለቤትነት በመምራት ከዳር ማድረስ እንደሚገባው የመንግስት ኮምዩኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ጥሪ አቀረበ።ጽህፈት ቤቱ \"ድሎቻችንን መጠበቅ የሁላችንም ድርሻ ነው!\" በሚል ርዕስ ለኢዜአ በላከው ሳምንታዊ የአቋም መግለጫ እንዳለው መላው ኢትዮጵያዊ በመንግሥት የተጀመረውን የጸረ-ኪራይ ሰብሳቢነት ትግል በመቀላቀልና በባለቤትነት በመምራት ከዳር ማድረስ ይገባዋል።የአገሪቷ ሠላም በአስተማማኝ መልኩ እንዲጠበቅና የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ዕድገቶች እንዲፋጠኑ የኪራይ ሰብሳቢት አመለካከትና የጸረ ሠላም ኃይሉን በአስተማማኝ ሁኔታ መመከት አስፈላጊ ነውም ብሏል።ለዚህም ሁሉም ዜጋ እንደ ወትሮው ሁሉ በመንግሥትና በመላው ኅብረተሰብ በሚካሄደው የተቀናጀና የጋራ ርብርብ የራሱን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቋል።( ኢዜአ)የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-ድሎቻችንን መጠበቅ የሁላችንም ድርሻ ነው!የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የራሳቸውን ጉዳይ በራሳቸው፣ የአገራቸውን ጉዳይ ደግሞ በጋራ የሚወስኑበትን ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መስርተው መተዳደር ከጀመሩ አስርተ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ የቅራኔ ምንጮች የነበሩ ጉዳዮችን ሁሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በመዝጋታቸውም አገራችን ኢትዮጵያ ሰላም በራቀው የአፍሪካ ቀንድ እየኖረች በአንጻራዊነት ከመቼውም ጊዜ የተሻለች ሰላማዊት አገር መሆን ብቻ ሳይሆን ለሌሎች አገራትም የሰላም ዘብ መሆን ችላለች።ህዝቦቻችን ሰላም በማግኘታቸውም ሙሉ ትኩረታቸውን ወደ ልማት በማዞር ልማታቸውን እያፋጠኑና ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጡ ይገኛሉ። የልማቱ ድምር ውጤትም አገራችንን በማያቋርጥ ፈጣን የኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ምህዋር ውስጥ እንድትገኝ አስችሏታል። ይህም ለዘመናት ትታወቅበት የነበረውን መጥፎ ገጽታ ቀይሮት በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ ካሉ የዓለም አገራት በግንባር ቀደምትነት ተጠቃሽ አገር አድርጓታል። ከድህነትና ኋላቀርነት የምትላቀቅበትና ወደከፍታ ማማ የምትወጣበት ጊዜ ሩቅ አለመሆኑንም በተግባር ማረጋገጥ ችላለች።እነዚህና ሌሎችም በርካታ ድሎች የመመዝገባቸውን ያህል ግን በየጊዜው የተከሰቱ ፈተናዎችም አጋጥመዋል። ዋናው ነገር ያጋጠሙንን ችግሮች ሁሉ በመንግሥትና በህዝቦቻችን የጋራ ትግል እየፈታናቸው መምጣታችን ነው።አሁን ባለንበት ወቅትም ቢሆን የሰላማችንን፣ የፈጣን ዕድገታችንን እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታችንን ሂደት እየተፈታተኑ ያሉ እንቅፋቶችን ፊት ለፊት እየተጋፈጥን ነው የምንገኘው፡፡ ህዝባችንን እያማረሩ ያሉ የመልካም አስተዳደር፣ የኪራይ ሰብሳቢነት፣ የፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ሌሎችም  በጥልቅ ተሃድሶ እንቅስቃሴ የተለዩ ልዩልዩ ችግሮች በሚፈቱበት አግባብ ላይ አቅጣጫ ተቀምጦ ወደሥራ ለመግባት ተሞክሯል። ከተከናወኑት አበረታች ሥራዎች መካከልም በወጣቶች ላይ በስፋት የሚታየውን የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ እና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት የተደረጉ ጥረቶችን በአብነት ማንሳት ይቻላል። የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታትም እንቅስቃሴዎች የተደረጉ ሲሆን የህብረተሰቡን እርካታ ማረጋገጥ ይቀረናል በሚል ተጨማሪ ሥራዎችን በመስራት ላይ እንገኛለን።ይህ በእንዲህ እንዳለ የሥርዓቱ ጤናማ ሆኖ መቀጠል የግል ጥቅማቸውን እንደሚያቋርጠው የተረዱ ያለአግባብ የመበልጸግ ፍላጎት ያላቸው ሃይሎች ከጸረ ሰላም ሀይሎች ጋር በመቀናጀት የተጀመረውን ትግል ለማፈን ሲፍጨረጨሩ ታይተዋል። በሰላማዊ ህዝቦች መካከል ቅራኔን እስከመፍጠርና የአገራችንን ሰላም እስከማደፍረስ ብሎም ገጽታዋን እስከማበላሸት የቻሉትን ሁሉ ለማድረግ ሞክረዋል።ከዚህ የምንረዳው ነገር ቢኖር በኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባሮቹ ላይ የተጀመረው አገራዊ ትግል የአገራችን እና የህዝቦቿ ህልውና ጉዳይ መሆኑን ነው። እንደዚያው ሁሉ ብሄር ተኮር ግጭቶች እንዲከሰቱና አለመረጋጋት እንዲኖር ምክንያት የሆኑትን ሃይሎች ለማስወገድ የተጀመረውን ትግል ከዳር ማድረስ ለመንግሥት አካላት ብቻ የሚተው ተልዕኮ አለመሆኑንም በውል መገንዘብ ያሻል።የአገራችን ሰላም በአስተማማኝ መልኩ እንዲጠበቅ፣ የተጀመረው ተስፋ ሰጪ እድገታችን እንዲፋጠን ብሎም ፈጣኑን የእድገት ጉዟችንን ለመቀልበስ እየተፍጨረጨረ ያለውን የኪራይ ሰብሳቢ እና የጸረ ሰላም ሃይል በአስተማማኝ ሁኔታ ድባቅ መምታት የሚቻለው እንደወትሮው ሁሉ በመንግሥትና በመላው ህዝባችን በሚካሄድ የተቀናጀና የጋራ ርብርብ ብቻ ነው። በመሆኑም መላው የአገራችን ህዝቦች፣ በመንግሥት የተጀመረውን የጸረ- ኪራይ ሰብሳቢነት ትግል እንደወትሮው ሁሉ በመቀላቀልና በባለቤትነት በመምራት ከዳር እንዲያደርሱትና ለድል እንዲያበቁት መንግሥት ጥሪውን ያቀርባል። ያስመዘገብናቸውን ድሎች መጠበቅና ማስቀጠል የምንችለው እንደወትሮው ሁሉ በህዝቦቻችን የላቀ ተሳትፎና ባለቤትነት ብቻ ነውና!", "passage_id": "058e8c5d63da981cf6647f82e3ac9fb9" }, { "passage": "የሰማእታት አደራን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ኪራይ ሰብሳቢነትና ሙስናን ከምንጩ ማድረቅ እንደሚገባ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ አስታወቁ።ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ፣የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝና የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ከሜቴ አባላት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት ) የትጥቅ ትግል የጀመረበትን የደደቢት በርሃ ትናንት ጎብኝተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ደደቢትን ከጎበኙ በኋላ እንዳስገነዘቡት የስርአቱ አደጋ የሆነውን ኪራይ ሰብሳቢነትና ሙስናን በፅናት በመታገል የሰማእታት አደራን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ወቅቱ የሚጠይቀውን መስዋእት መክፈል የግድ ነው።ውድ ታጋዮች ህይወት የሰጡበትን አላማ ለማሳካትና መልካም አስተዳደር ለማስፈን ጸረ ዴሞክራሲ አሰራርን በፅናት መታገል እንደሚገባም አሳስበዋል።የትግሉ ፋና ወጊ በሆነው በደደቢት በርሃ  የተገኙት ለተራ ጉብኝትና ሽርሽር ሳይሆን ” በሺህ የሚቆጠሩ ታጋዮች ህይወት የከፈሉለትን አላማ በማሳካት የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት ቃል ለመግባት ነው” ሲሉ አስገንዝበዋል።የትግራይ ቆይታቸው ለየት ያለ ስሜት፣ለየት ያለ ፅናት፣ለየት ያለ የትግል ወኔና ለየት ያለ መስዋእት መክፈል እንደሚያስፈልግ ያዩበትና የተገነዘቡበት ሳምንት እንደነበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።ህወሓት ያሳለፋቸውን ውጣ ወረዶችና እልህ አስጨራሽ የትግል ጉዞ አስመልክቶ የትጥቅ ትግሉ በተጀመረበት በደደቢት በርሃ ለተገኙ የአገሪቱ ፕሬዜዳንትና የኢህአዴግ የሥራ አስፈፃሚ ኮሜቴ አባላት የድርጅቱ ነባር ታጋይ አቶ አባይ ፀሃየ፣አቶ ስብሓት ነጋና ሁለት ነባር ሲቪል አባላት ማብራሪያ ተሰጥተዋል።ከነባር ታጋዮቹ መካከል አቶ አባይ ፀሀየ “በጥቂት ተማሪዎች የተጀመረው ትግል ፍሬ አፍርቶ ህወሓት አእላፍን በማሰለፍ ለድል የበቃና እንደወርቅ በእሳት ተፈትኖ ያለፈ ድርጅት ነው” ብለዋል።አቶ ስብሓት ነጋ በበኩላቸው ህልውናውን ለማጥፋት ከተቃጣው መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ ድርጅቱ ራሱን በመከላከል አሁን ለደረሰበት ደረጃ መድረሱን ተናግረዋል።የድርጅቱ ነባር አባል አቶ ካህሳይ ገብረመድህን ከምስረታው ጀምሮ እስካሁን የህዝብ ክንፍ በመሆን በፅናት የታገሉ መሆኑን ገልጸው የላቀ የህዝብ ፍቅር ላለው ድርጅት የበኩላቸውን ድርሻ በብቃት መወጣታቸውን አስታውቀዋል።የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከሽሬ ወደ ደደቢት በርሃ ሲያመሩ የየአካባቢው ሕዝብ ደማቅ አቀባበል እድርጎላቸዋል።(ኢዜአ)", "passage_id": "0ba94772d126bf2567566a2521c9d55f" }, { "passage": "-የኢህአዴግ 10ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ  መልካም አስተዳደርን በተመለከተ ባደረገው ጥልቅ ውይይት ህዝቡ በየደረጃው የሚያነሳቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አመራሩ በቁርጠኝነት ለመፍታት የሚያስችለውን አቅጠጫ አስቀመጠ፡፡በጉባኤው ላይ እንደተገለፀው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ከላይ እስከ ታች ያለው አመራር በቁርጠኝነት መስራት አለበት፡፡ ችግሩን ለመፍታት የውስጠ ድርጅት ትግልን ማጠናከር እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን በተጨማሪም በየደረጃው ያሉ አደረጃጀቶችና የሚዲያ ተቋማት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በሚደረገው ትግል የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ለማድረግ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባም ተመላክቷል፡፡ችግሩን ለመፈታት ድርጅትና መንግስት ከሚያደርጉት ጠንካራ ትግል በተጨማሪ ህዝቡ የችግሩ የመፍትሄ አካል ለማድረግ ጠያቂና ምክንያታዊ ማህበረሰብ ለመፍጠር መረባረብ እንደሚገባም ተጠቁሟል፡፡የመልካም አስተዳደር ችግርን ለመፍታት የህዝቡ ተሳታፊነትና ቁርጠኝነት ምቹ ሁኔታ መሆኑን ያስገነዘቡት የኢህአዴግ ሊቀመንበር ጓድ ኃይለማርያም ደሳለኝ ‹‹ይህን ሞጋችና በምክንያት የሚደገፍና የሚቃወም ሚዛናዊ ህዝብ ይዘን የህዝባችንን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ደረጃ በደረጃ በጊዜ የለኝም መንፈስ እልባት መስጠት ይገባል›› ብለዋል፡፡የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳይ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለይደር የሚቀመጥና በለዎሳስ የሚያዝ ባለመሆኑ ኢህአዴግ ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚሰራበት መሆኑን በጉባኤ ተሰምሮበታል፡፡‹‹ህዝባዊ አደራን በላቀ እድገትና ትራንስፎርሜሽን›› በሚል መሪ ሃሳብ በመቐለ ከተማ እየተካሄደ ያለው የኢህአዴግ አስረኛው ድርጅታዊ ጉባኤ አሁንም በሁለት ቀን ውለው በማክሮ ኢኮኖሚ፣ የመሰረት ልማትና ማህበራዊ ልማት ጉዳዮች ላይ በጥልቀት የመከረ ሲሆን በዛሬው ዕለት  የኦዲት ቁጥጥር ሪፖርት እንዲሁም የድርጅቱን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀ መንበር በመምረጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡", "passage_id": "fb10719ce6816dd1afa7189a59dd4704" }, { "passage": "ሙስናን ለመዋጋትና አህጉሪቱን ከችግሩ ለማውጣት የየሃገራቱ መሪዎች በጋራና በቅንጅት መስራት ይኖርባቸዋል ሲሉ ከተለያዩ ሃገራት የተውጣጡ እና  የ30ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ተሳታፊዎች አሳሰቡ፡፡ህብረቱ በአህጉሪቱ የተንሰራፋውን ሙስና ለመከላከል  የያዝነውን የፈረንጆቹ 2018  በአህጉሪቱ የፀረ ሙስና ዘመቻ አመት እንዲሆን ማወጁ ይታወሳል፡፡ይህ የህብረቱ ውሳኔ በትክክል ተግባራዊ ተደርጎ የሚሳካ ከሆነ በአህጉሪቱ ለሁሉም ችግሮች መንስዔ የሆነውን ሙስናን መቀነስ እንደሚቻል ነው የጉባዔው ተሳታፊዎች የገለጹት፡፡በጉባዔው ላይ የተሳተፉት የቡርኪናፋሶው ተወካይ በአህጉሪቱ ለሚስተዋሉ ግጭቶች፣ ረሃብና የከፋ ድህነት ዋነኛው መንስዔ ሙስና ነው ብለው ሙስናን መከላከል ደግሞ ከመሪዎች መጀመር ይኖርበታል ብለዋል፡፡ሌላኛው የጉባዔው ተሳታፊ ግብጻዊ በበኩላቸው ሙስና ከደቡብ አፍሪካ እስከ ግብጽ እንደ ካንሰር የተንሰራፋ የአህጉሪቱ ችግር ነው ሲሉ ገልጸውታል፡፡አያይዘውም ሙስና እጅግ በርካታው የአህጉሪቱ ህዝብ በድህነት ውስጥ ሳለ ጥቂቶች ብቻ ሃብቱን የሚዘርፉበት ነው ብለው ይህን ለመግታት የተደረገ ጥረት አለመኖሩ ሙስናው አሁን ለደረሰበት አስከፊ ደረጃ አድርሶታል፡፡በመሆኑም የየሃገራቱ መሪዎች ከልባቸው ሆነው ሊታገሉት እንደሚገባ አስምረውበት ሃሳባቸውን አጠቃለዋል፡፡የማዕከላዊ አፈርካዋ ተሳታፊ ደግሞ አፍሪካ ከፍተኛ የተፈጥሮ ሃብት የታደለች ብትሆንም አለመታደል ሆኖ አብዛኛው ህዝቧ ከድህነት ወለል በታች ይገኛል ካለች በኋላ ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ምክንያት ሙስና እንደሆነም ገልጻለች፡፡ ", "passage_id": "5a08af1f5cf624cc9ea8b283151cf578" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- በአገር አቀፍ ደረጃ በሎጂስቲክስ ዘርፍ የሚስተዋሉትን ችግሮች ቅንጅታዊ አሰራርን በማስፈን መፍታት እንደሚገባ ተገለፀ፡፡ የ‹‹አዲስ ወግ፤አንድ ጉዳይ›› የውይይት\nመርሐ ግብር ትናንት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በአገራዊ የሎጂስቲክስ ዘርፍ ሪፎርም ላይ በመከረበት ወቅት የትራንስፖርት ሚኒስትሯ\nወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ እንዳሉት፤የሎጂስቲክስ ዘርፍ የበርካታ ባለድርሻ አካላትን ትስስሮ መስራት የሚጠይቅ በመሆኑ የዘርፉ ተዋንያን\nበቅንጅት መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሎጂስቲክስ የማምረት፣ የማከማቸትና\nየማሰራጨት ተግባራትን አካቶ የያዘ ዘርፍ በመሆኑ ውጤታማነቱም በእነዚህ ተግባራት ላይ የተሰማሩ አካላትን ቅንጅት ይጠይቃል ያሉት\nሚኒስትሯ፣ በዚህም ከመንግሥት የሚጠበቁ ኃላፊነቶችን ከማሟላት ባሻገር በሎጂስቲክስ ዘርፍ የተሰማሩ የግል ባለሀብቶችን ማበረታታትና\nለአጠቃላይ አገራዊ ምጣኔ ሀብት እድገት የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ማድረግ እንደሚጠበቅበት አስታውቀዋል፡፡ ሐገር በቀል የኢኮኖሚ\nማሻሻያ መርሐ ግብሩን ለማሳካት የሎጂስቲክስ ዘርፉን ማዘመን አስፈላጊ መሆኑን ተናግረው፣መንግሥት ለዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም\nገልጸዋል፡፡በዘርፉ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ብሔራዊ የሎጂስቲክስ ስትራቴጂ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁንም ወይዘሮ ዳግማዊት ጠቅሰዋል፡፡\nየማሪታይም ጉዳዮች ባለስልጣን ዋና\nዳይሬክተር አቶ መኮንን አበራ ሎጂስቲክስ ጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራርን የሚጠይቅ ዘርፍ መሆኑን ጠቁመው፣ ዘርፉ ውጤታማ እንዲሆን የገንዘብ፣\nየመረጃና የግብይት ፍሰትን አቀናጅቶ መምራት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡ ‹‹ብሔራዊ የሎጂስቲክስ ስትራቴጂ መጽደቁ ጥሩ ጅምር\nነው፤የጠራ ራዕይና ግብ ለመንደፍ ያስችላል›› ያሉት አቶ መኮንን፣ ስትራቴጂውን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመተግበር የሚያስችል አደረጃጀት\nመፍጠር እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ባሕር ትራንዚትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ በበኩላቸው\nበሎጂስቲክስ አስፈጻሚና ተቆጣጣሪ እንዲሁም ደጋፊ ተቋማት መካከል ያለውን መስተጋብር ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተው፣የመሰረተ ልማትና\nየፋይናንስ አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በወጪና ገቢ ንግድ በኩል ካሉት የሎጂስቲክስ\nችግሮች መካከል ዋነኛው የፋይናንስ አቅርቦት ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣የሎጂስቲክስ ፋይናንስ ተቋማት እንዲኖሩ የሚያስችል\nአደረጃጀት መፍጠር ላይ ማተኮር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሎጂስቲክስ መምህር ዶክተር ማቴዎስ ኢንሰርሙ እንደሚሉት፤ የሎጂስቲክስ\nዘርፍ ችግሮች በወቅቱ ምላሽ ካላገኙ ውስብስብነታቸው ጨምሮ በአገራዊ ኢኮኖሚያዊ እድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራሉ፡፡ በተለይ\nየውጭ ምንዛሪ እጥረት ለዘርፉ እድገት መሰናክል ይሆናል፡፡ የአገሪቱን የሎጂስቲክስ ዘርፍ አፈፃፀምና ውጤታማነት ለማሻሻል የሎጂስቲክስ\nመሰረተ ልማቶችን በአገሪቱ አካባቢዎች ማስፋፋት እንዲሁም የዘርፉን የሰው ሀብት ልማት በማሳደግ በቴክኖሎጂና በፈጠራ እንዲታገዝ\nማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡አዲስ ዘመን የካቲት 28 ቀን 2012 ዓ ም አንተነህ ቸሬ", "passage_id": "60a4ec40e8f4047e186b1eee31069338" } ]
5c79fa87fc512e0781ea25a3dd0d013b
a68fd598cb6283e863eb3601fc7f7dde
በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር ላይ የተከሰተው ችግር የሀገራቱን ወዳጅነትና ትስስር እንደማያሻክረው ተገለፀ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና የሱዳን ግንኙነት እርስ በርሱ የተጋመደ በአብሮነትና በወንድማማችነት መሰረት ላይ የተገነባ በመሆኑ ከሰሞኑ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ የተከሰተው ችግር የሀገራቱን ወዳጅነትና ትስስር እንደማያሻክረው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ። አቶ ደመቀ መኮንን ሁለተኛው የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳዮች የከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት ጉባኤ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት፤ የኢትዮ ሱዳን የሁለትዮሽ ግንኙነት በአብሮነትና በወንድማማችነት መሰረት ላይ ለረጅም አመታት የተገነባ በመሆኑ ከሰሞኑ በድንበር ላይ የተፈጠረው ክስተት ከሁለቱ ህዝቦች ፍላጎት በተቃራኒው የሆነ ተግባር ነው። የሱዳን ወታደሮች በአካባቢው ላይ በወሰዱት እርምጃ የአርሶ አደሮች ምርት በእሳት ቃጠሎ ደርሶበታል፣ ከመኖሪያ ቦታቸውም ተፈናቅለዋል፤ ንጹሐን ዜጎች ሕይወታቸው አልፏል። በአዲስ አበባ በተደረገው ስብሰባ ላይ ውጤታማ ውይይቶች ተደርገው ከስምምነት መደረሱን ያስታወሱት አቶ ደመቀ፤ በድንበር አካባቢ ያለው የጸጥታና የሰላም ጉዳዮችን በጋራ ለመፍታትና የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ መልካም ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በቅርቡ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ የተከሰተው ችግርም የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች የሁለትዮሽ ግንኙነት እንደማያሻክረው ነው የገለጹት። እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ፤ ሱዳን ከዓለም አሸባሪነት መዝገብ ዝርዝር ውስጥ በአሜሪካ መንግስት በመሰረዟ ሱዳን ከአጋር ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላት ሲሆን፤ ይሄም የህዝቦቿን ልማት እና ዕድገት እውን ለማድረግ እገዛው የጎላ ይሆናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37922
[ { "passage": "ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር አልፋ እንድትጠብቅም ሆነ መሬት እንድትይዝ የተደረሰ ስምምነት እንደሌለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ጥር 12/ 2013 ዓ. ም በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።ስለ ኤርትራና ሶማሊያ ሰራዊትስለ ህዳሴ ግድቡመንግሥት ህግ ማስከበር በሚለው ወታደራዊ ዘመቻ የመከላከያ ሰራዊት ወደ ሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ባቀናበት ወቅት ድንበር አካባቢ ሊከሰቱ የሚችሉ የደህንነት ስጋቶችን በተመለከተ ከሱዳን ጋር መግባባት ተደርሶ ነበር ብለዋል።\"ድንበር አካባቢ የሁለቱን አገሮች ደህንነት የሚጎዳ እንቅስቃሴ እንዳይኖር በኛ አመራር ለሱዳን መንግሥት አደራ ተሰጥቷል\" ያሉት ቃለ አቀባዩ አክለውም ሆኖም \"ድንበሩን አልፈው አገራችን ግቡ መሬት ይዛችሁ ጠብቁልን የሚል አይነት ሊኖር የሚችል አይደለም፤ አልነበረም\" ብለዋል።ከሰሞኑ የሱዳን ምክር ቤት ጄኔራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን ሱዳን ሰራዊቷን ወደ ድንበር ያስጠጋችው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ዐብይ አህመድ ጥያቄና ፈቃድ ነው መባሉ ተዘግቧል።ለዚህም ምላሽ የሰጡት ቃለ አቀባዩ \"ቅዠት ነው\" ካሉ በኋላም \"አጥፊ ኃይሎች የናንተን ድንበር ተጠቅመው ወደኛ ድንበር እንዳይገቡ ማለት ኑና ገብታችሁ ጭራሽ ያልተከለለና መቶ አመት በዚሁ ሁኔታ ይሁን ተብሎ የቆየውን መሬት ድንበር የኛ ነው በሉ ማለትም አይደለም\" ብለዋል።ከዚህም ጋር ተያይዞ በአመራር ደረጃ የተደረሰ ስምምነት እንዳለ መነገሩ ስህተት ነው ብለዋል።በአሁኑ ወቅት በሁለቱ አገራት መካከል የድንበር ይገባናል ውጥረት እየተጋጋለ ነው በተባለበት ወቅትም የመንግሥታቸውን አቋም ያስረዱት አምባሳደር ዲና፤ ሱዳን በትግራይ ክልል ግጭት ከተነሳበት ከሶስት ቀናት በኋላ፣ ከጥቅምት 27፣ 2013 ዓ.ም ያላግባብ የያዘችውን መሬት ትልቀቅና ወደ ንግግር እንግባ የሚል ነው። የሱዳን የማስታወቂያ ሚኒስትር ከጥቂት ሳምንታት በፊት ለሮይተርስ ዜና ወኪል እንደተናገሩት የአገራቸው ሠራዊት ግዛቴ ነው ከሚላቸው ቦታዎች ውስጥ አብዛኛውን መቆጣጠሩንና ይህም የማይቀለበስ እርምጃ መሆኑን መግለፃቸው የሚታወስ ነው።ሁለቱን አገራትን በተመለከተም የድንበር፣ የቴክኒክና ከፍተኛ ኮሚሽኖች ያሉ ሲሆን በየጊዜው ውይይቶችም ሲደረጉ እንደነበር አንስተዋል።ሁለቱን አገራት ለማስታረቅና ለማሸማገል የተለያዩ አካላትም ጥረት እያደረጉ መሆናቸውን የጠቀሱት አምባሳደር ዲና \"አገሮቹን እናደንቃቸዋለን፤ ይኸንን ያሰቡትን ጥሩ ነው እንላለን። ነገር ግን እኛ እኮ እምቢ አላልንም። እንነጋገር ነው እያልን ነው ያለነው። ያስቀመጥነው ቅድመ ሁኔታ ግን ወደነበራችሁበት ተመለሱና እንነጋገር የሚል ነው\" ብለዋል።ጉዳዩ ያሳሰባት የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ኢትዮጵያና ሱዳን ያላቸውን የድንበር ላይ ውዝግብ በሰላማዊ መንገድና በውይይት እንዲፈቱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣችው መግለጫ ጠይቃለች።ቃለ አቀባዩ በመግለጫቸው ወቅት አፅንኦት ሰጥተው የተናገሩት ሱዳን የያዘችውን መሬት እንድትለቅ ኢትዮጵያ በቅድመ ሁኔታ ማስቀመጧንና ይህ ከተሳካ ሁለቱ አገራት በዋናነትም ችግራቸውን ተነጋግረው መፍታት እንደሚችሉም አስረድተዋል።የሱዳንና የኢትዮጵያ ታሪካዊ፣ ምጣኔ ኃብት፣ ባህላዊና የህዝቦች ትስስርና ቁርኝት በመጥቀስም አገራቱ ወደ ግጭት ቢገቡም የሁለቱም ህዝቦች እንደሚጎዱ አፅንኦት ሰጥተዋል።በታሪካቸውም እንዲሁ ከመደጋገፍና ከመረዳዳት በስተቀር ይህ ነው የሚባል ግጭት ተከስቶ እንደማያውቅ የተናገሩት አምባሳደር ዲና በተለይም በሰላም ጥበቃ፣ ከደቡብ ሱዳን ጋር ያላቸውን ግጭት ለመፍታትና በአጠቃላይ የሱዳንና ሰላምና መረጋጋት ለማምጣት ኢትዮጵያ ጉልህ ሚና ተጫውታለች ብለዋል።የህዝቦቹን ቁርኝትና የአገራቱንም እጣ ፈንታ አንድ መሆኑን አፅንኦት በመስጠትም አሁን ሱዳን እያደረገችው ያለችው ከህዝቡ የመነጨ አይደለም ይላሉ። \"የሁለቱ አገራት ጥቅም ይተሳሰራል ስንል ግጭቱ ሁለቱንም አገራት እንደሚጎዳ እናውቃለን። ነገር ግን ሁለቱን አገሮች አባልቶ የራሳቸውን ጥቅም በመሃል መፍጠር የሚፈልጉ ወገኖች እንዳሉ እናቃለን።\" ብለዋል።ቃለ አቀባዩ ሶስተኛ ወገን የሚሉትን አካል ባይጠቅሱም ሁለቱን አገራት በማበጣበጥ የሚጠቀሙ ኃይሎች አሉ በማለት የተናገሩ ሲሆን ግጭቱ የሱዳን ፍላጎት አይደለም ብለዋል።አምባሳደሩ የኢትዮጵያ መንግሥት \"አጥፊ ኃይሎች\" ያላቸው አካላት በሱዳን ድንበር በኩል እንዳይገቡ ሲል አገራቱ ካላቸው ትስስር አንፃር እምነት በመጣል እንደሆነም ጠቆም አድርገዋል። \"የፌደራሉ መንግሥት እምነት በሱዳን አለው እንጂ ከኋላ ይወጉናል የሚል እሳቤ በኢትዮጵያ በኩል እንዳልነበረ ነው። እንዲህ አይነት ተግባር ከጀርባ ይፈፅማሉ ብለንም ከኢትዮጵያ በጭራሽ ግምት አልነበረም። ያየነው ግን ተቃራኒውን ነው\" ብለዋል።በዚሁ መግለጫ ላይ ትግራይ ላይ በተደረገው ወታደራዊ ግጭት የኤርትራ ሰራዊት ተሳትፏል ስለመባሉም ምላሽ ሰጥተዋል። ሁኔታውንም \"ፕሮፓንዳና መሰረተ ቢስ ነው\" ብለውታል።ከኤርትራም በተጨማሪ የሶማሊያ ሰራዊት ተሳትፏል መባሉን ሃሰት ነው ብለዋል።የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የአገሩን ዳር ድንበር ማስጠበቅ ብቻ ሳይሆን በሶማሊያ፣ በሩዋንዳ፣ በብሩንዲና፣ ኮንጎ \"ትልቅ ገድል የሰራ ኃይል ነው\" በማለትም የሰራዊቱን ጥንካሬ አስረድተዋል።\"የውስጥ የህግ በላይነትን ለማስከበር ማንንም አገር የሚጠራ አይደለም፤ የሚጠራም አገር የለም፤ ሊጠራም አይችልም፤ አይገባም፤ አይፈልግምም፤ አስፈላጊም አልነበረም\" በማለት አፅንኦት በመስጠትም ነው የተናገሩት።ቢቢሲ ያናገራቸው የትግራይ ክልል ነዋሪዎች፣ አዲስ የተሾሙት የመቀሌ ከንቲባም ሆኑ፣ የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ሌሎች አካላት የኤርትራ ወታደሮች መሳተፋቸውን ቢናገሩም አምባሳደሩ በበኩላቸው ግጭቱን ቀጠናዊ ለማድረግና ጣልቃ ገብነትን ለመጋበዝ የተቃጣ ነው ብለውታል።ወደ አስመራ የተወነጨፉት ሮኬቶችም ይህንኑ ለማገዝና የኤርትራ ሰራዊት እንዲገባ በሚል ታቅዶም ነው ብለዋል።ነገር ግን ወደ ኤርትራ ሚሳይል ሲወነጨፍ አገራቱ ካላቸው ርቀት አንፃር የኤርትራ ሰራዊት ድንበር አካባቢ ድንበሩን ለማስከበር ሊታይ እንደሚችል ጠቁመዋል።\"ይህንን ወስዶ ከመከላከያ ሰራዊት ጎን እየተዋጉ ነው ማለት ስህተት ነው። የኤርትራም የሶማሊያም ሌላ ኃይል አልነበረም። ብቃት አለው በራሱ ነው የጨረሰው\" ብለዋል።ነገር ግን የአውሮፓ ሕብረት በከፍተኛ ዲፕሎማቱ ጆሴፕ ቦሬል በሰጠው መግለጫ \" ግጭቱ ወደ ቀጠናዊ ወደ መሆን የመሸጋገር እድል አለው፣ ለምሳሌ የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ግጭት ውስጥ መሳተፋቸው፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከሶማሊያ መውጣታቸው\" በማለት መጥቀሳቸው የሚታወስ ነው። አምባሳደር ዲና በበኩላቸው በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ሚዲያውም ሆነ የምዕራቡ አለም ግጭቱን ቀጠናዊ ለማድረግ ሲሰሩ የነበሩ ኃይሎች ነበሩ ብለዋል።በርካታ የጦር መሳሪያ አምራችና ሻጮች ጠመንጃ ከመሸጥ ጀምሮ እንዲሁም ግጭቶችን ሰበብ በማድረግ እርዳታ እስከማሰባሰብ ድረስ በአፍሪካ ከሚከሰቱ ጦርነቶች የሚጠቀሙ ኃይሎችም እንዲሁ ግጭቱ የቀጠናዊ መልክ እንዲኖረው ጥረዋል ብለዋል።\"ንግድ ስለሆነ በየሚዲያውም ቀጠናዊ ለማድረግ እያራገበ ይገኛል፤ የምዕራቡ አለም ከግጭቱ መጠቀም ለሚፈልጉ በርካታ አገራት እንዲበጣበጡ ይፈልጋሉ ያሉት ቃለ አቀባዩ \"ግጭቱ ቀጠናዊ ሳይሆን ከሽፏል\" በማለትም ያለውን ፖለቲካ አስረድተዋል።ሌላኛው ከሶስትዮሽ ህዳሴ ግድቡ ጋር ተገናኝቶ የተናገሩት አምባሳደር ዲና በህዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ ቀጥሎ ተጠቃሚዋ ሱዳን ናት ብለዋል።የህዳሴ ግድብ መሰረት በተጣለበት ወቅት ከሶስቱ አገራት የተውጣጣ ነፃ አለም አቀፍ የባለሙያዎች ጉባኤ ቡድን ግድቡ በከባቢ፣ ምጣኔ ኃብትና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል የሚለውን አጥንቶ በግምገማው መሰረትም አይጎዳም የሚል ማጠቃለያ ላይ መድረሱንን አስታውሰዋል።ሱዳን የህዳሴ ግድብ በደለልና በጎርፍ መጥለቅለቅን ከማስቀረት በተጨማሪ፣ ርካሽ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚነት፣ የዳበረ እርሻ እንዲሁም ደለል ለመጥረግ ከምታወጣው ወጪም እንደምታተርፍ ሱዳን ታውቃለች የሚሉት አምባሳደር ዲና፤ \"የሚያነሷቸው ነገሮች የነሱ አይደሉም፤ ሌላ አካል ወክለው ነው እየሰሩ ያሉት\" ይላሉ።በኢትዮጵያ በኩል አሁንም የተቀየረ ነገር እንደሌለና ድርድሩም ሆነ ግንባታና ሙሌቱ ተያይⶋ ይቀጥላልም በማለት የመንግስታቸውን አቋም አስረድተዋል።", "passage_id": "18e9d92874b88677f3306bc3f4859fcb" }, { "passage": "አዲስ አበባ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባሳለፍነው ሐሙስ በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ላይ ተፈጥሮ በነበረው ግጭት በደረሰው ጉዳት የተሰማውን ሐዘን ገለፀ፡፡\nሚኒስቴሩ ትናንት ባወጣው መግለጫ ግንቦት 20 ቀን 2012 ዓ.ም በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር አካባቢ በተከሰተው ግጭት የተሰማውን ሃዘን ገልጾ፣ በአደጋው ሰለባ ለሆኑ ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝቷል፡፡\nሁለቱ አገራት የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ እና ለማጣራት በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ አመልክቷል፡፡\nበአጎራባች የአካባቢ እና የክልል አስተዳደሮች መካከልም ያለው የተቀናጀ ትብብር ቀጣይነት እንዲኖረው ጥሪ አስተላልፏል፡፡\nችግሮቹ በተሻለ ሁኔታ መፍትሔ የሚያገኙት በሁለቱ አገራት መካከል ባለው መልካም፣ ወዳጃዊ እና ሰላማዊ ግንኙነት ላይ በመመርኮዝ እንደሆነም በመግለጫው አስታውቋል፡፡\nይህ ክስተት በሁለቱ አገራት ህዝቦች መካከል ያለውን ጠንካራ ግንኙነት እንደማይወክልም ያለውን የፀና እምነት ገልጿል ፡፡\nበሁለቱ አገራት መካከል መልካም ግንኙነትን እና መግባባትን መሠረት ያደረገ የረጅም ጊዜ ግንኙነቶችን የሚያንፀባርቅ ጠንካራና ወዳጃዊ አካባቢን የበለጠ ማጎልበት አስፈላጊ መሆኑም ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 24/2012በጋዜጣው ሪፖርተር", "passage_id": "0724d939da9bff564fe1eba6533c7158" }, { "passage": "በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት መቋጨቱ እንዳስደሰታቸው አስተያየታቸውን ለዋልታ የሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ነዋሪዎቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ወደ አስመራ የልዑካን ቡድኑን መርተው በመሄድ ለብዙ አመታት ተራርቆ የኖሩትን ወንድማማች ህዝቦች እንዲስማሙና በዜጎቹ መካከል መልካም ግንኙነት እንዲኖር ማድረጋቸው ትልቅ ደስታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡ለዋልታ አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ሃምሳ አለቃ ሞገስ ሞኮንን ከዚህ በፊት በነበረው የድንበር ግጭት የሁለቱ ሀገራት ህዝቦች አብረው መኖር እያማራቸው ለብዙ አመታት ተለያይተው የቆዩ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ግን ሰላም ተፈጥሮ የሁለቱ ሀገራት ባንድራ ባንድ ላይ ተውለብልቦ ማየት ባጣም ደስ እንዳሰኛቸው ገልጸዋል፡፡ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ፋሲል ንጉሴ በበኩላቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ በፊት የገቡትን ቃል በተግባር እያሳዩ መሆናቸውን ገልጸው የኤርትራ ህዝቦች አቀባበልም በህዝቦች ዘንድ ያለውን አብሮ የመኖር ፍላጎት እንደሚያሳይና በበኩሉ ያልጠበቀው ነገር እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡የሁለቱ ሀገር ዜጎች ተዋደውና ተፋቅረው የሚመላለሱበትና በጋራ የሚሰሩት መንገድ የምከፍት እንደሆነም አስተያየት ሰጪዎቹ አንስተዋል፡፡ነዋሪዎቹ የሁለቱ ሀገራት ስምምነት የምስማሙበትና የምፈልጉት በመሆኑ በደስታ እንደምደግፉም ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "fd4d5c808933c6648935d7a3c0fa700a" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 27 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ጦርነት ለኢትዮ ሱዳን የድንበር ልዩነቱ መፍትሄ አይደለም ብላ እንደምታምን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለፁ።ቃል አቀባዩ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ሳምንታዊ ጋዜጣዊ መግለጫ  ሰጥተዋል።በመግለጫቸው ከኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ጋር በተያያዘ ያለውን ጉዳይ የሚከታተል የድንበር ኮሚሽን እና ባለሙያዎች መኖራቸውንም ተናግረዋል፡፡አሁን ላይ ኢትዮጵያ ሃገራቱ ወደነበሩበት ውይይት እንመለስ የሚል አቋም እንዳላት ያነሱት ቃል አቀባዩ፥ ጦርነት ለድንበር ልዩነቱ መፍትሄ አይደለም ብላ ታምናለችም ነው ያሉት፡፡ሆኖም የድንበር ሉዓላዊነቷን ለማሥከበር ጠንካራ ስራዎችን ታከናውናለች ብለዋል ቃል አቀባዩ።አምባሳደር ዲና በመግለጫቸው ለአንድ ወር ተቋርጦ የነበረው የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ውይይት ተጠናክሮ መቀጠሉን አንስተዋል።በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊመቀንበር በደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ የተሰየሙ ባለሙያዎች ባቀረቧቸው ሰነዶች ላይ ውይይት እየተካሄደ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።ባለፈው እሁድ በነበረው የሶስትዮሽ ውይይት መቋጫ ላይ በቀረበው ሰነድ ላይ ኢትዮጵያና ሱዳን ሲስማሙ ግብፅ አልተስማማችም ብለዋል።እሁድ በነበረው ውይይት ላይ ሀገራቱ እስከአሁን የነበሯቸውን ልዩነቶች እና ስምምነቶች ባለሙያዎች እንዲያቀርቡ በሚል ውይይቱ ቢቋጭም በትናንትናው ዕለት ሱዳን ባለመገኘቷ ውይይቱ አለመካሄዱንና  ጉዳዩን በተመለከተም ለሰብሰቢዎቹ ሪፖርት መደረጉን አስረድተዋል።ዛሬን ጨምሮ በቀጣይ ቀናት  ሱዳን በውይይቱ ላይ ለምን እንዳልተገኘች መልስ ትሰጣለች ተብሎ እየተጠበቀ መሆኑንም አምባሳደሩ አስታውቀዋል።ነገር ግን በህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሚካሄደው የሶስትዮሽ ውይይት አሁንም ይቀጥላል ነው ያሉት አምባሳደር ዲና።በፍሬህይወት ሰፊው", "passage_id": "7774f28176ffc20cfed78a938a966ada" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥር 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ ድንበር ኮሚሽን በዛሬው ዕለት ተቀማጭነታቸው በሱዳን ለሆኑ ዲፕሎማቲክ ሚሽኖች፣ ቆንስላዎች እና የዓለምአቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ገለፃ አድርጓል።መድረኩ ላይ የተገኙት በሱዳን የኢ.ፌ.ድ.ሪ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው የድንበር ጉዳይ ባሉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እና የጋራ የድንበር መድረኮች አማካኝነት በሰላማዊ መንገድ መፈታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።በዚህ ረገድ ከዳግልሽ ተራራ በስተሰሜን ከሰፈራ እና ከእርሻ መሬት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ እንዲመጣ የሚደነግገው እና በሁለቱ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በፈረንጆቹ ሐምሌ ወር 1972 የተደረገው የማስታወሻ ልውውጥ ከፍ ያለ ፋይዳ ያለው እንደሆነ በአጽንኦት አስረድተዋል።አያይዘውም በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ በተቀመጠው መሰረት የጉዊን መስመርን ዳግም ማካለል ከመጀመሩ በፊት ከዳግልሽ ተራራ በስተሰሜን ከእርሻ መሬት እና ሰፈራ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት የጋራ ልዩ ኮሚቴው ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ ያካተተ ሪፖርት ለጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቅረብ እንደሚኖርበት ገልጸዋል።ምንም እንኳ የጋራ ልዩ ኮሚቴው ሁለቱን ሀገሮች የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ ለማቅረብ ስምንት ዙር ስብሰባዎችን ቢያካሂድም ኃላፊነቱን ገና እንዳላጠናቀቀ ጠቁመዋል።በተጨማሪም አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ የኢትዮጵያ-ሱዳን ድንበር የጋራ ልዩ ኮሚቴ ስራ ባልተጠናቀቀበት ሁኔታ እና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥቅምት ወር መጨረሻ ህግ ለማስከበር ወደ ትግራይ ክልል ያደረገውን ስምሪት እንደ መልካም አጋጣሚ መጠቀሙን አንስተዋል።በዚህ መሰረት የሱዳን ሰራዊት ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ በመግባት ንብረት ከመዝረፉ፣ ወታደራዊ እና የእርሻ ካምፖችን ከማቃጠሉ ባሻገር በኢትዮጵያውያን ላይ እስራት፣ ጥቃት እና ግድያ መፈጸሙ እንዲሁም በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ማፈናቀሉን ጠቅሰዋል።ይኸውም የ1972 የማስታወሻ ልውውጥን በግልጽ የጣሰ ተግባር መሆኑን አስረድተዋል።አምባሳደሩ አክለውም በሁለቱ እህትማማች ሀገራት ጸንቶ ከቆየው አጋርነት እና ትብብር መንፈስ በተቃረነ መልኩ አጋጣሚውን በመጠቀም የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ሰራዊት ለቋቸው የወጣ ካምፖችን መቆጣጠሩን ገልጸዋል።አምባሳደሩ በተጨማሪም ሱዳን በችግር ውስጥ በነበረችበት ጊዜ ሁሉ ኢትዮጵያ ከሱዳን ህዝብ ጎን መቆሟን አውስተው፣ ኢትዮጵያ በውስጥ ጉዳይዋ በተጠመደችበት ወቅት ከሱዳን ሰራዊት የደረሰባት ጥቃት የሚገባት እንዳልነበረ መግለፃቸውን ከኤምባሲው ያገኘኘው መረጃ ያመለክታልአምባሳደሩ በገለጻቸው አክለውም የማስተካከያ እርምጃ በፍጥነት ካልተወሰደ፣ ታይቶ የማይታወቀው የሱዳን ሰራዊት ተግባር የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ብሎም የጋራ ድንበሩን ዳግም የማካለሉን ስራ የሚያወሳስብ እና ለሁለቱ ሀገራት ህዝቦች እንዲሁም ለቀጠናው ከፍ ያለ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚኖረው መሆኑን አንስተዋል።አምባሳደሩ የኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ልዩነቱን ሁለቱ ሀገራት በገቧቸው ስምምነቶች እና ባሉ የጋራ የድንበር መድረኮች መሰረት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ኢትዮጵያ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።አምባሳደሩ አክለውም ለችግሩ ዘላቂ እልባት ለመስጠት፡ አንደኛ፣ የሱዳን ሰራዊት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፈጸመውን ወረራ በመቀልበስ በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ በተቀመጠው መሰረት ወደ ቅድመ-ህዳር 2020 እንዲመለስ፣ሁለተኛ፣ ወደ ድንበር ዳግም ማካለል ከመገባቱ በፊት የጋራ ልዩ ኮሚቴው በ1972 የማስታወሻ ልውውጥ መሰረት ከዳግሊሽ ተራራ በስተሰሜን ከሰፈራ እና እርሻ መሬት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ የማቅረብ ስራውን እንዲያጠናቅቅ፣ሶስተኛ፣ የጋራ ድንበሩን ዳግም ለማካለል ሁለቱ ሀገራት ያቋቋሟቸው የጋራ የድንበር ኮሚሽን፣ የጋራ የቴክኒክ የድንበር ኮሚቴ፣ እና የጋራ ልዩ ኮሚቴ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እና ስራቸውን እንዲያጠናቅቁ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተዋል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን! ", "passage_id": "9660e485a92d6ef7070029e28872b1cf" } ]
0603eedd69c17ccca8353f068fa845d6
2c71ad83faf2bc0c36890bc46df99a28
‹‹የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪን ለማሻሻል የዘርፉን ቴክኖሎጂ ወደአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ለውጦ መጠቀሙ ፋይዳው የላቀ ነው››ዶክተር አስረግደው ካሳ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀድሞው አጠራሩ የህንጻ ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር
አስቴር ኤልያስ አዲስ አበባ፡- የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪን ይበልጥ ለማሻሻልና ለማስፋፋት የዘርፉን ቴክኖሎጂ ከአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ መጠቀሙ ፋይዳው የላቀ ነው ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀድሞው አጠራሩ ህንጻ ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር ዶክተር አስረግደው ካሳ ገለጹ፡፡ዶክተር አስረግደው ካሳ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ቴክኖሎጂን በተመለከተ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ በአሁኑ ወቅት በዘርፉ እየወጡ የሚገኙ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪን እያሻሻሉ ሲሆን፤ የሚወጡትን ቴክኖሎጂዎች ደግሞ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ መጠቀሙ ጠቀሜታው ጉልህ ነው። ቴክኖሎጂን መጠቀም ያለምንም ጥያቄ ፋይዳው ከፍ ያለ ስለመሆኑ አያጠራጥርም ያሉት ዶክተር አስረግደው፣ በአሁኑ ወቅት ያሉትም ቴክኖሎጂዎች ቢሆኑ የትየለሌ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።በተለይም ከምርታማነት፣ ከደህንነት፣ ከጥራት፣ ከጊዜ፣ ከዋጋ፣ የግንባታን ሂደት ቀድሞ ከማየት አንጻር እንዲሁም ከሌሎች በርካታ ሁኔታዎች አኳያ ቴክኖሎጂ ወሳኝ ስለመሆኑ የሚያጠያይቅ ጉዳይ አይደለም ብለዋል።እንደ ዶክተር አስረግደው ገለጻ፤ የቴክኖሎጂው ጠቀሜታ በስራ ላይ ስህተቶች እንዳይከሰቱ ከማድረጉም በተጨማሪ ድግግሞሾች እንዳይኖርም ጭምር የሚያደርግ ነው።ቴክኖሎጂን መጠቀም መቻል የተዋጣለት ዲዛይንም እንዲኖር በማድረጉ በኩል ከፍ ያለ ሚና ይጫወታል።የስራውን ሂደት የተሳለጠ በማድረጉም በኩል ድርሻው ጉልህ ነው።ስለዚህ የተሻለ ውጤትን ለማግኘት እና የተሻለ አሰራርን ለመቀየር የሚያስችል ነው፡፡እንዲህ ሲባል ግን ትልቁ እና ማስተዋልን የሚጠይቀው ነገር ቴክኖሎጂውን ወደራሳችን ነባራዊ ሁኔታ ማምጣቱ ላይ ነው ያሉት ዶክተር አስረግደው፤ ቴክኖሎጂውን ወደአገራችን በምናመጣት ጊዜም ጥንቃቄ ማድረጉ መልካም ነው ሲሉ አስረድተዋል።ተማሪውም፣ ድርጅቶችም ሆኑ የተለያዩ ተቋማት የሰለጠነው ዓለም የሚጠቀምበትን ቴክኖሎጂ ወደራሱ በማምጣት አሰራሩን ሊያበለጽጉለት እንዲችሉ ሲያደርግ የአገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ መሆን ይኖርበታልም ብለዋል።እርሳቸው እንዳሉት፤ ቴክኖሎጂን አምጥቶ መጠቀሙ መልካም ነገር ነው፤ ነገር ግን የምናመጣውን ቴክኖሎጂ መልሰን ከአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ምርምር በማድረግ እና በጥናት በማስደገፍ ማላመድ ተገቢነት ያለው አካሄድ ነው።የሚመጣው ቴክኖሎጂ ከጊዜው ጋር የሚሄድ መሆኑን ማረጋገጥ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ውጤታማ የሚያደርግ ነው።ቴክኖሎጂን የማላመዱ ሂደት ከትምህርት ቤት መጀመሩ ደግሞ የፈጠራ ክህሎታቸውን ስለሚጨምር ተማሪዎችን የመፍትሄ ሰዎች ያደርጋቸዋል፡፡ተማሪዎች ገና ከመጀመሪያው ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማመቻቸቱ ሁሌም የሌሎች አገሮችን ቴክኖሎጂ አምጥተን ከማላመድ ሊያላቅቀን በመቻሉ ነው ሲሉም አክለዋል።የሌሎች አገሮችን ቴክኖሎጂ ለማላመድ በሚደረገው ጥረት መሰላቸትን ሊያመጣ ስለሚችል ከዚህ አይነት መሰላቸት ለመላቀቅ በራስ ወደተፈጠሩ መሄድን ከወዲሁ መጀመሩ ተገቢነት አለው ብለዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37854
[ { "passage": " ኢኮኖሚውን በጠንካራ መሰረት ላይ ለመጣልና ኢንዱስትሪ መር መዋቅራዊ ሽግግሩን ለማፋጠን በሳይንስና ቴክኖሎጂ የተደገፉ ምርምሮችና ፈጠራዎች ሚና የላቀ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ፡፡በኢኮኖሚ ያደጉትና የበለጸጉት አገራት ዛሬ ለደረሱበት ደረጃ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ምርምሮች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመው የኢትዮጵያን የህዳሴ ጉዞ ለማፋጠንና ኢንዱስትሪ መሪ ኢኮኖሚን ለመገንባት ለዘርፉ ትኩረት መሰጠቱን አስታውቀዋል፡፡በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ የተለየ ክህሎትና ዕውቀት ያላቸው ተማሪዎች አቅማቸውን ይበልጥ ለማጎልበት እንዲረዳቸው በፌዴራል ደረጃ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለማደራጀት መታቀዱን አስገንዝበዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት መንግስት ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በሰጠው ትኩረት የአዳማና የአዲስ አበባ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች በዘርፉ ጥራት ያላቸውን ባለሙያዎች እንዲያፈሩ በአዲስ መልክ ተደራጅተዋል፡፡በተያዘው ዓመትም በበዮ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ብቻ 100 ሚሊዮን ብር ተመድቧል፡፡ አገራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራና ስርፀት አቅምን ለማጎልበት አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ያደርጋል፡፡ የፈጠራ ባለሙያዎችን የማበረታትና የመደገፍ ጥረቱም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አቶ አቢይ አህመድ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ለአገር ልማትና ዕድገት የሚጫወተው ሚና እጅጉን የላቀ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም በዘርፉ አገራዊ ምርምርና የፈጠራ አቅምን ማሳደግ ተገቢ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ መር ለማሸጋገር የነደፈችውን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ቁልፍ መሳሪያ በመሆኑ መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል፡፡መንግስት ለምርምርና ስርፀት አስፈላውን ድጋፍና ትብብር በማድረግ ዘርፉ እንዲጠናከር የሚጠበቅበትን እያበረከተ ነው ብለዋል፡፡ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የሳይንስ መረጃ መደላደል እንዲፈጠር ከማድረጉም በላይ አምስት ሚሊዮን ብር ያህል ድጋፍ ማደረጉንም አስገንዝበዋል፡፡የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ተማሪዎችና መምህራን፤ ሰልጣኞችና አሰልጣኞች እንዲሁም ተመራማሪዎችን በማበረታታት ችግር ፈች ምርምሮችና ፈጠራዎች በብዛት እንዲወጡ እንደሚያስችል ነው ሚኒስትሩ የገለጹት፡፡በላፉት አምስት ዓመታት በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ዘርፍ በአጠቃላይ አንድ ሺ 418 ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞች፣ ተመራማሪዎችና የፈጠራ ባለሙያዎች መሸለማቸው ተገልፇል፡፡ዘንድሮ በተካሄደው ስድስተኛው የሳይንስ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ባለሙያዎች ሽልማት በአጠቃላይ 278 የፈጠራ ባለሙያዎች የተሸለሙ ሲሆን 207 በአጠቃላይ ትምህርት፣57 የቴክኒክና ሙያ፣ ስድስት ተመራማሪዎችና ስምንት የፈጠራ ባለሙያዎች ናቸው፡፡ ከእነዚህም 21 ነጥብ አምስት በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው፡፡ለተሸላሚዎቹ የነሃስ፣የብር፣የወርቅ ሜዳሊያና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡", "passage_id": "b268227a8e5df29e8ab3e8106ee9c951" }, { "passage": "– በኢትዮጵያ የግንባታውን ዘርፍ በአግባቡ እንዲመራ የሚያደርግ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ልማት ረቂቅ ፖሊሲና የማስፈጸሚያ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀቱን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ከባለድርሻ አካላት ጋር በረቂቅ ሰነዶቹ ላይ ለመምከር ዛሬሰኔ10/2005 በተዘጋጀው አገር አቀፍ አውደ ጥናት ላይ ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ኃይሌ እንደገለጹት ኢንዱስትሪው በአገሪቱ የህዳሴ ጉዞ ላይ ልዩ ሚና ያለው የልማት ዘርፍ ነው፡፡በአገሪቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለመንገድ፣ ለባቡር መስመር እና ለሌሎች የኢኮኖሚ መሰረተ ልማቶች ቁልፍ ሚና የሚጫወተው የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ዘርፍ ፖሊሲና የሕግ ማዕቀፉ ከመዘጋጀቱ በፊት ችግሮቹ በጥናት መለየታቸውንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡የኮንስትራክሽን ዘርፍ የፋብሪካ ውጤቶችን ከ30 እስከ 60 በመቶ ወጪ የሚጠይቅ የግንባታ ቁሳቁሶችን እንደሚጠቀም የጠቆሙት ሚኒስትሩ በአገሪቱ ኢንዱስትሪውን ለማስፋፋት ፖሊሲውና የሕግ ማዕቀፉ ማስፈለጉን ተናግረዋል፡፡በዘርፉ ተዋናይ የሆኑ ባለሞያዎችን ያሳተፈ በአግባቡ የተደራጀና ኃላፊነቱን የሚወጣ የጋራ መድረክ መፍጠር አንዱ የፖሊሲው አቅጣጫ መሆኑን ጠቁመው የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱንም አስገንዝበዋል፡፡የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ መዘጋጀቱን አመልክተው በፕሮጅክት አፈጻጸም ላይ የሚታዩ የአቅም ውሱንነትን ለመቀነስ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምክክር መቅረቡንም አስታውቀዋል፡፡በምክክር መድረኩ ተሳታፊ የሆኑ የክልልና የፌደራል መንግስት ተጠሪዎች፣ የትምህርትና የምርምር ተቋማት እና ሌሎች  ባለድርሻ አካላት በቀረቡ የፖሊሲና የሕግ ማዕቀፎች ላይ ገንቢና የማሻሻያ ሃሳቦችን በማፍለቅ እንዲያዳብሯቸውም አሳስበዋል፡፡የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር ደኤታው ኢንጂነር ኃይለመስቀል ተፈራ በአገሪቱ የኮንስትራክሽን ዘርፍ የመንገድና የባቡር፣ የኃይል ማመንጫና የመስኖ ግድብ ስራ፣ የስኳር ኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ መሰረተ ልማት ፕሮግራሞች፣ የመጠጥ ውሃ ግንባታዎች፣ የጤናና የትምህርት ተቋማት እንዲሁም በግል ባለሃብቶች የሚገነቡ የማምረቻና አገልግሎት መስጫ ተቋማት በየጊዜው እያደገ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡ሚኒስትር ዲኤታው ኢንጂነር ኃይለመስቀል ተፈራ በአሁኑ ወቅት በአስርና በስድስት ደረጃዎች በተከፋፈሉ ምድቦች ውስጥ በአገሪቱ በድምሩ 2 ሺህ 500 የግንባታ ስራ ተቋራጮች መመዝገባቸውን ጠቁመው ከ230 በላይ የአማካሪ መሃንዲስ ድርጅቶች ተመዝግበው በስራ ላይ መስማራታቸውን አስታውቀዋል፡፡እንደ ኢሬቴድ ዘገባ ከ47 ሺህ በላይ የዲዛይንና የኮንስትራክሽን ባለሙያዎች  በአገሪቱ ተመዝግበው በልማቱ ተሳታፊ መሆናቸውን ገልጸው በዘርፉ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል በግልጽና በተጠያቂነት መርሆ ላይ የተመሰረተ ውስጣዊ ጠንካራ አስራር ስርዓት ለመዘርጋት በፖሊሲውና የሕግ ማዕቀፉ መመራት ግድ ይላል ብለዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡", "passage_id": "c38d00263a5130f018c8a2697ca76a69" }, { "passage": "አዲስ አበባበኮንስትራክሽን ማኑፋክቸሪንግና በሲሚንቶ ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት መኖሩ ለሲሚንቶ ኢንዱስትሪዎች ቁልፍ ማነቆ መሆኑ ተገለጸ። የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ሃላላ በሸራተን ሆቴል የሲሚንቶ ቴክኖሎጂ መሪ መዛኞችና ባለሙያዎች የማጠቃለያ መርሃ ግብር በተካሄደበት ወቅት እንደተናገሩት በዘርፉ ከፍተኛ የሆነ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት መኖሩ ለኢንዱስትሪው ማነቆ ሆኗል። ችግሩን ለመፍታትም ለዘርፉ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም የኢንዱስትሪ ዩኒቨርሲቲ ትስስሩን የበለጠ ማጠናከርና በሀገሪቱ ከሚገኙ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆችና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል። ከደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ ጋር በትብብርበተዘጋጀው መድረክ ላይ የሲሚንቶ ቴክኖሎጂ መሪ መዛኞችና ባለሙዎችን በማስመዘንና ስልጠና በማስጀመር ሂደት የተገኙ ውጤቶችና ያጋጠሙ ችግሮችን የሚመለከት ሪፖርት ቀርቦ ከሲሚንቶ ፋብሪካዎች ባለቤቶችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዶበታል። ሪፖርቱን ያቀረቡት የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የኮንስትራክሽን ዘርፍ ቡድን መሪ አቶ ግርማ ለማ ችግሩ የተፈጠረው በሀገሪቱ ባሉ በሁሉም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆችና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኮንስትራክሽን ማኑፋክቸሪንግና በሲሚንቶ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ምንም ዓይነት የትምህርትና የስልጠና መስክ ባለመኖሩ ነው ብለዋል። በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በሲሚንቶ ቴክኖሎጂና በማቴሪያል ሳይንስ የልቀት ማዕከል ለማቋቋም የተጀመሩ ሥራዎች ቢኖሩም ወደ ሥራ ባለመግባታቸው ዘርፉን መደገፍ አልቻሉም። በመሆኑም የሲሚንቶ ማሰልጠኛ ማዕከላትና የስልጠና ማቴሪያሎች አለመኖራቸው ለሲሚንቶ ኢንዱስትሪው ማነቆ ሆኖበት ቆይቷል። ኢንስቲትዩቱ ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲና ልምድ ካላቸው የሙገር፣ መሰቦ፣ ደርባና ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ባለሙያዎችና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ጋር በመተባበር የሲሚንቶ ቴክኖሎጂ ሞዴል ካሪኩለም ተዘጋጅቷል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ለዘርፉ ትኩረት ሰጥተው መስራት የሚገባቸው መሆኑን አመላክተዋል። የደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅና ሲሚንቶ ዘርፍ ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ኃይሌ አሰግዴ በበኩላቸው በዘርፉ ያለውን የሰለጠነ ሰው ኃይል እጥረት ችግር ለመፍታት በሀገሪቱ ውስጥ የሲሚንቶ ቴክኖሎጂ የልህቀት ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል አንድ ተቋም ሊኖር የሚገባ መሆኑን አመላክተዋል። ለዚህም በዘርፉ የተሰማሩ የሲሚንቶ ኢንዱስትሪ ባለሀብቶችና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ለነገ ሳይሉ ቅድሚያ ሰጥተው መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 15/2011 በይበል ካሳ", "passage_id": "eeb78b283554a1a570aef79b7296ae21" }, { "passage": " ኢዜአ፡- የዩኒቨርሲቲ- ኢንዱስትሪ ጥምረት የመፈላለግ ግንኙነትን መሰረት ያደረገ ባለመሆኑና በዕቅድ ባለመመራቱ ምክንያት ውጤታማ ሊሆን አለመቻሉን የቤቶች ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስታወቀ።ሚኒስትሯ ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች ተቀናጅተው ባለመስራታቸው ምክንያት ብቁ የሰው ሃይል እየተመረተ አይደለም።በዚህም ምክንያት ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቆ የሚወጣው የሰው ሃይል አንፃራዊ እውቀት ቢይዝም፤ ”እስካሁን በነበረው አሰራር በስራ ላይ ውጤታማ ሊያደርግ የሚችል ክህሎት ግን ይዞ እየወጣ አይደለም” ብለዋል።”እንደ ሃገር እስካሁን ስንከተለው የነበረው የዩኒቨርስቲ -ኢንዱስትሪ ግንኙነት ትክክል ያልሆነና በእቅድ ያልተደገፈ ነው” ሲሉም ተናግረዋል።በመሆኑም የትምህርት ተቋማቱ የሰው ሃይል የማስተማሩን ስራ እየሰሩ ተማሪዎቹ የክህሎት ልምምድ እንዲያገኙ ኢንዱስትሪዎችን የሚጠይቁበት ሁኔታ ቀርቶ የመፈላለግ አሰራር መፈጠር እንዳለበት ገልፀዋል።ይህን ለማስተካከል መጀመሪያ ሁሉም የመንግስት ተቋማትና የግል ኢንዱስትሪ ተቋማት በሚሰሩት የስራ ልክ የሚፈልጉትን የሰው ሃይል በቁጥርና በሚፈልጉት የእውቀት አይነት ለይተው ለትምህርት ተቋማቱ ማሳወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።በዚህ መሰረት ዩኒቨርስቲዎች የተጠየቀውን የሰው ሃይል በሚፈለገው የእውቀት አይነትና ልክ ማሰልጠን ኢንዱስትሪዎችም ለጠየቁት የሰው ሃይል የክህሎት ስልጠና እንዲያገኙ ማለማመድ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።በተለይ እንደ ሃገር በርካታ የስራ እድል ለመፍጠር ትኩረት በተሰጠው የኮንስትራክሽኑ ዘርፍ ይህ ተግባራዊ እንዲሆን ሚኒስቴሩ ድልድይ ሆኖ እንደሚሰራ ገልጸዋል።በዩኒቨርሲቲና ኢንዱስትሪ መካከል\nያለውን ግንኙነትና ትስስር\nበማጠናከርና ግንኙነቱን በዕቅድ በመምራት በተለያዩ ዘርፎች ውጤት ሊያመጣ የሚችል የሰው ሃብት ለማልማት በትኩረት መሰራት እንዳለበትም ኢንጂነር አይሻ ጠቁመዋል።የዩኒቨርሲቲ – ኢንዱስትሪ ትስስር የተጀመረው በቅርብ ቢሆንም አሁንም በሚፈለግበት ደረጃ አልደረሰም፡፡ለችግሩ መንስዔ ናቸው ከሚባሉት ውስጥ ኢንዱስትሪዎች የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገድ እንዲሁም በአብሮነት ምርምር ለማድረግ ፍላጎት ማጣት እንደምክንያት ጠቅሰዋል።ትምህርት ሚኒስቴር በ2010 ዓ.ም ማገባደጃ ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ የመምህራንም ወደኢንዱስትሪ ቀርበው ራሳቸውን ለማብቃትና ለመማር ግዴታ አለብኝ ብሎ አለማሰብ አንዱ ክፍተት መሆኑን መግለጹ ይታወሳል፡፡አዲስ ዘመን ጥር 14/2012", "passage_id": "b2435f8506129710862ba132ed333e96" }, { "passage": "ታምራት ተስፋዬአዲስ አበባ፦ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማትን ተጠቅሞ ድህነትን ለማሸነፍና ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋገር የእቅድ ተግባራዊነትን ማረጋገጥና እስከዛሬ ከተመጣበት የተለየ መንገድን መከተል እንደሚያስፈልግ ተገለጸ። የ2013 የመጀመሪያ ዙር ሀገር አቀፍ ሞዴል የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዐውደ ርእይና ባዛር በአዲስ አበባ ከተማ ጀሞ አንድ ትናንት በተከፈተበት ወቅት፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ፣ “የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማትን ተጠቅመን ድህነትን ለማሸነፍ ብሎም ወደ ኢንዱስሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋገር የያዝነውን እቅድ ተግባራዊነት ማረጋገጥና እስከዛሬ ከመጣንበት የተለየ መንገድን መከተል ግድ ይላል›› ብለዋል።የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራ ከሰዎች ህልውና ጋር የተያይዘ በመሆኑ ኃላፊነቱ ከባድ መሆኑን ያስገነዘቡት ሚኒስትሯ፣ በአሁንም ወቅትም ‹‹ከዩኒቨርሲቲና ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተመርቀው ሥራ እንዲፈጠርላቸው የሚጠብቁ ዜጎች በርካታ ናቸው፣ በዘርፉ የታቀፉና በስኬትና በውድቀት መካከል የሚንገዳገዱ አንቀሳቃሾችን ህልውን መታደግም ሌላው ፈታኝ የቤት ሥራ መሆኑን አመልክተዋል። ከፍተኛ የህዝብ ሀብት ፈሶባቸው የሚገነቡ የመስሪያና መሸጫ ቦታዎች ሠርተው የዕለት ጉርሳቸውን ለመሙላት ለተዘጋጁ ዜጎች በፍትሐዊነት ተደራሽ ማድረግም ከእያንዳንዱ የሚጠበቅ ኃላፊነት መሆኑን ያመላከቱት ኢንጂነር አይሻ፣ በአደራ የተቀበልነውን የህዝብ ገንዘብና መነሻ ጥሪት ለሌላቸው መገኖቻችን ያለ እጅ መንሻና ያለ ውጣ ውረድ በብድር ማቅረብም ለድርድር የማይቀርብ ግዴታችን ነው ብለዋል።ኃላፊነቱ ለአንድ ወገን የሚተው ባለመሆኑም አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት ከወትሮው በተለየ መጠናከውና መተባበር እንዳለባቸው አመልክተው ፣ ሞዴል የጥቃቅንና አነስተኛ አነቅሳቃሾችም መንግሥት በሚያደርገው የገበያ ትስስርና ድጋፎች ሳይወሰኑ በየትኛውም ገበያ ውስጥ ገብቶ የመወዳደርና ብቃት ማዳበር እንዳለባቸው አስታውቀዋል። መንግሥታዊ ድጋፎች የሚደረጉት\nአንቀሳቃሾቹ በሁለት እግራችው\nእስኪቆሙ እንጂ ዕድሜ ልክ አለመሆኑን በመረዳት እስከዛሬ የመጡበትን የአሸናፊነት፣ የመለወጥና ድህነትን ድል የመንሳት ፅናት እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል።በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዣንጥራር ዓባይ በበኩላቸው፣ ‹‹በትምህርት ገበታ መምጠቃቸው፣ ዲግሪና ማስትሬት መጎናፀፋቸው፣ ሳያስኮፍሳቸው ቀን ከሌት ሠርተው፣ የላብና ወዛቸውን ፍሬ በሚያጭዱ፣ የሥራ ክቡርነት በተግባር በተገለጠበት መስክ በኩራት የተሰማሩ በርካታ ዜጎች በዘርፉ ፈርተዋል›› ብለዋል።ለዚህ ስኬት የበቁበት መንገድ ቀናና ምቹ እንዳልነበር አፅእኖት የሠጡት አቶ ዣንጥራር፣ ከመደራጀት ጀምሮ በስትራቴጂ ላይ የተቀመጡና መብታቸው የሆነውን መንግሥታዊ ድጋፍ በተገቢው መንገድ ለማግኘት ብዙ ፈተናዎች መጋፈጣቸውን አስታውሰዋል። ጥቃቅን ከሚለው ስያሜ አንስቶ የምርት፣ ግብአትና የገበያ እጥረት የማምረቻና መሸጫ ቦታ በተገቢው አለመመቻቸታቸውና የኪራይ ሰብሳቢነት ተግዳሮቶች በመንገዳቸው በብርቱ እንደፈተናቸው ተናግረዋል።ኃላፊው፣አነቀሳቃሾቹ መሰል ፈተናዎችን ተቋቁመው ለስኬት መብቃታቸውን በማድነቅም፣ ‹‹ልፋታቸው ፍሬ እንዲያፈራ፣ ድካማቸው ከራስ አልፎ ለወገን እንዲተርፍ፣ የሥራ ተነሳሽነታቸው ለብዙዎች አርአያ ሆኖ አገር እንድትኮራ የከተማ አስተዳደሩ ምንጊዜም ከጎናቸው እንደሚሆንም ማረጋገጫን ሰጥተዋል።‹‹በቀጣይም ዜጎችን ከማደራጀት ጀምሮ መንግሥታዊ ድጋፎችን ውጤታማ ለማድረግ እስከአሁን የመጣንበትን አሠራር በመፈተሸና አዳዲስ አሠራሮችን በመተግበር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንሠራለን›› ብለዋል።የፌዴራል የከተሞችና የሥራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር፣ አቶ ገብረ መስቀል ጫላ በበኩላቸው፣ በዐውደ ርእይና ባዛር ላይ ከመላ አገሪቱ ከ200 በላይ ሞዴል ጥቃቅንና አንስተኛ ኢንተርፕራይዞች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን መስፋፋት መከላከል በሚያስችል መልኩ እንዲሳተፉ መደረጉን አስታውቀዋል።‹‹ዘላቂነት ያለው የገበያ ትስስር ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለኢንተርፕራይዞች ልማት መሰረት ነው›› በሚል የተዘጋጀው\nዐውደ ርእይና ባዛር ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር ይፈጠራል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ እስከ ገና ዋዜማ ክፍት ሆኖ ይቆያል።አዲስ ዘመን  ታህሳስ 23/2013", "passage_id": "688f20052a291fb9b6c71c49a686f9c3" } ]
b0d021ed4d037a52d01b43663561fc3e
bbbc4c2d3b2fa90eddb12059dc7bd956
በየዕለቱ ከ300 በላይ የኮቪድ ታማሚዎች ወደ ጽኑ ህክምና እንደሚገቡ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ
 ፋንታነሽ ክንዴአዲስ አበባ፡- በየቀኑ ኮቪድ-19 ከሚገኝባቸው ሰዎች ውስጥ ከ300 በላይ የሚሆኑት ጽኑ ህክምና የሚያስፈልጋቸው መሆናቸውን እና ከእነዚህ ውስጥ እስከ 50 የሚደርሱት የመተንፈሻ አካልን የሚረዳ ማሽን የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ይህን ተከትሎም ለስድስት ወራት የሚቆይ ኮቪድ 19ን የመከላከል ንቅናቄ ሊያካሂድ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት በኮቪድ የሚሞቱና ጽኑ ህክምና የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡ በየቀኑ ቫይረሱ ከሚገኝባቸው ሰዎች ውስጥ ከ300 በላይ የሚሆኑት ጽኑ ህክምና የሚያስፈልጋቸው ሲሆኑ፤ ከዚህ ውስጥ ከ40 እስከ 50 የሚሆኑት ደግሞ የመተንፈሻ አካልን የሚረዳ ማሽን ያስፈልጋቸዋል፡፡ በየቀኑ የሚገለጸው ቁጥር ምርመራ ከተደረገላቸው ውስጥ ብቻ ስለሆነ ትክክለኛውን ቁጥር አያሳይም ያሉት ዶክተር ደረጀ፤ አሁን እየተመረመረ ያለው በቀን ከ4ሺ እስከ 5ሺ ሰው በመሆኑ አሁን ከሚመረመረው በሶስትና አራት እጥፍ ከፍ ቢደረግ ውጤቱም በተመሳሳይ ከፍ ማለቱ እንደማይቀር ተናግረዋል። ከዚህ በፊት በሽታው የሚገኘው በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች እንደነበረና አሁን ላይ ግን ከ900 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች ላይ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች እንደተገኙም ገልጸዋል። ከዚህ በፊት ከተመረመረው ከሶስት እስከ አራት በመቶ ብቻ ቫይረሱ የሚገኝባቸው እንደነበርና አሁን ግን ከ10 እስከ 15 በመቶ በአንዳንድ ቦታዎች ላይም ከ30 እስከ 40 በመቶ ቫይረሱ እየተገኘ መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ ዶክተር ደረጀ ገለጻ፤ ቀደም ሲል አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጆ ትልቅ ስራ ባይሰራ ኖሮ አሁን ላይ የሚኖረው ከዚህ የከፋ ይሆን ነበር። የአዋጁን መነሳት ተከትሎ ምክር ቤቱ መመሪያዎች እንዲወጡ በመፍቀዱ መመሪያዎች እንዲዘጋጁ ተደርጓል። በመመሪያው ላይ ለህብረተሰቡና ለሚመለከታቸው አካላት ግንዛቤ መፈጠሩንም ተናግረዋል። የጤና ሚኒስቴር ያወጣውን መመሪያ ተመስርተውም በትራንስፖርት፣ በትምህርትና ቱሪዝም ዘርፎችም የየራሳቸውን መመሪያ እንዲያዘጋጁ የተደረገ ቢሆንም፤ በሚፈለገው ደረጃ ተግባራዊ አልተደረገም። በመመሪያው ላይ የህግ ክፍተት ባይኖርም፤ መተግበር ላይ ግን ክፍተቶች ተስተውለዋል። በህብረተሰቡ ዘንድ ህግን ተቀብሎ ተግባራዊ ለማድረግ ተነሳሽነት እየታየ አለመሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ከታች እስከ ላይ ያለው የመንግስት አመራርም መመመሪያውን እያንዳንዱ ቦታ ላይ እንዲተገበር በማድረግ በኩል ቸልተኝነትና የቁርጠኝነት ማነስ እንደሚስተዋልበት አስረድተዋል። የሃይማኖት ተቋማትና ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ በወጣው መመሪያ መሰረት ምን እየተሰራ እንደሆነ መከታተል ላይ ክፍተት መኖሩንም ገልጸዋል። ጸጥታ አካላትም መመሪያውን መሰረት አድርገው ህጉ ተፈጻሚ እንዲሆን በማድረግ በኩል ብዙ እንዳልሰሩበት አስረድተዋል። እንደ ዶክተር ደረጀ ገለጻ፤ የሚስተዋለውን ችግር ለመቅረፍ የስድስት ወራት ኮቪድን የመከላከል እቅድ አዘጋጅው ወደ ስራ ሊገቡ ተዘጋጅተዋል። በተለይ ማንም ሰው ማስክ ካላደረገ መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት አገልግሎት እንደማያገኝ አውቆ እንዲስተካል፤ የህግ አካላትም በዚህ ላይ እንዲሰሩና የራሳቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ፤ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ስራዎችን ማጠናከርና ህብረተሰቡን ለማስተማርና ለማንቃት ስለተወነ በቅርቡ ወደ እንቅስቃሴ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ሚዲያዎች ከዚህ በፊትም በራሳቸው ተነሳሽነት ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ አሁንም የሚችሉትን እንዲያደርጉና መንግስትም የሚችለውን ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅበት በመጠቆም፤ ወቅታዊ ነገር እንዳለ ሆኖ ኮቪድ ደግሞ ሌሎችንም ነገሮች ሊያበላሽ ስለሚችል ትኩረት ሰጥቶ መስራት የሚያስፈልግ በመሆኑ በየደረጃው ካሉ የመንግስት የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያዎች ጋር የተጠናከረ ስራ ለመስራት በእቅዳቸው ላይ ማስቀመጣቸውን ተናግረዋል። የሰዎች የመመርመር ፍላጎት መቀነስ፣ በመመርመሪያ ኪቶች ውድነትና በላብራቶሪ ስራ ላይ በሚሰሩ ባለሙያዎች በተወሰነ መልኩ እየታየ ባለው መሰላቸት ምክንያት በየዕለቱ የሚመረመሩ ሰዎች ቁጥር መቀነሱን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ትልልቅ አቅም ያላቸው ብዙዎቹ ከዚህ በፊት የተገዙና በእጃችን ላይ ያሉ የአሜሪካ ማሽኖች ከዛው ከካምፓኒው የሚመጣ ‹‹ቴስት ኪት›› የሚጠቀሙ በመሆናቸው ምርመራውን ለማሳደግ እንቅፋት ሆኗል ብለዋል። ከዛ ውጪ በአብዛኛው ጥቅም ላይ የሚውሉት አገር ውስጥ የሚመረተው ‹‹ቴስት ኪት›› መሆኑን እና ያሉ ችግሮችን በመፍታት በቀጣይ እስከ 10ሺ የሚደርስ ዕለታዊ ምርመራ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ ዶክተር ደረጀ ገለጻ፤ የጤና ባለሙያዎቻችን ምንም የተለየ ክፍያ ሳይከፈላቸው ለረጅም ጊዜ በርካታ ስራዎችን ሰርተዋል። በፌዴራል ደረጃ ቀጥታ በኮቪድ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች የተወሰኑ ድጋፎችን ለማድረግ ተሞክሯል። በክልል ደረጃ ግን ብዙ ገንዘብም ስለሚጠይቅ በሙላት አልተደረገም። ባለሙያዎች ስራ ላይ ሲያድሩ ግን አበል ይከፈላል። እናም አቅም በፈቀደ እሱን አሻሽሎ በመክፈል ለመደገፍ እና በዚህ ላይም ከክልሎች ጋር እየተወያዩ ይገኛል። በዚህ መልኩ መቀጠል ከባድ ስለሚሆንም ብዙ የሚሰሩ ሰዎችን በማሰልጠን በፈረቃ እንዲሰሩና ባለሙያውም ሳይደክመው የተወሰነ ሰዓት እንዲሰራ ለማድረግ በሁሉም ሆስፒታሎችና ቦታ ላይ ኮቪድን አቀናጅተው እንዲሰሩ የሚደረግም ይሆናል። ከዚህ ባለፈ አዲስ አበባ ላይ የተጀመረውን ከኮቪድ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ላላቸው ባለሙያዎች ከሚከፈላቸው ክፍያ ላይ ግብር እንዲቀር የማድረግ እርምጃ ወጥ የሆነ አሰራር እንዲኖር የሚያስችል መመሪያ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርበው ውሳኔ እየጠበቁ መሆኑን በመጠቆም፤ የመድህን ኢንሹራንስ ለሁሉም የሚሰራ መሆኑንና አንድ ሰው በኮቪድ ህይወቱ ካለፈ ለቤተሰብ ካሳ እንደሚከፈል እና ከዚህ በፊት በኮቪድ ምክንያት ህይወታቸው ላለፉ ባለሙያዎችና የአስተዳደር ሰራተኞች ክፍያ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል። በአጭር ጊዜ ውስጥ በአለም ላይ ተስፋ ሰጪ የሆኑ ክትባቶች እየተገኙ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ደረጀ፤ ለአዳጊ አገራት ከአለም ጤና ድርጅት ጋር በመሆን ሌሎች ያደጉ አገሮችም እየደገፉ ክትባቱን እንዲያገኙ ስለተወሰነ ኢትዮጵያም የሚገባትን ድርሻ እንደምታገኝ ገልጸዋል። ሆኖም ክትባቱ ለሁሉም ህዝብ የሚደርስ ስላልሆነ ለጤና ባለሙያዎች፣ በበሽታው ሊጎዱ የሚችሉ የተለያዩ በሽታዎች ላሉባቸው፣ በእድሜ ለገፉና ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅድሚያ እንደሚሰጥ አስረድተዋል። ሆኖም ክትባቱ ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት የሚተካ ስለማይሆን ክትባት መጣ ስለተባለ ለመከላከል የሚደረገው ጥንቃቄ ላይ ቸልተኝነት ማሳየት አገርን ዋጋ ሊያስከፍል ስለሚችል መጠንቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል። ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ ለ1ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ምርመራ የተደረገ ሲሆን፤ ከ120ሺህ በላይ ሰዎች በበሽታው ሲያዙ፤ 1ሺህ 860 በላይ ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው ማለፉን መረጃዎች ያሳያሉ።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37921
[ { "passage": "  - በሽታው በአጭር ጊዜ ውስጥ የመዛመት ዕድል አለው ተብሏል - ሰሞኑን በበሽታው መያዛቸው ከተረጋገጠባቸው ሰዎች መካከል አብዛኞቹ ከማህበረሰቡ ውስጥ የተገኙ ናቸው - ለበሽታው ስርጭት ከፍተኛ ተጋላጭነት እንዳላቸው የሚጠረጠሩ ተቋማት ላይ አሰሳ እየተካሄደ ነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በማህበረሰቡ ውስጥ ተሰራጭቷል የሚል ስጋት እንዳለ የገለፁት የጤና ባለሙያዎች፤ ይህም የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ፈታኝ እንደሚያደርገው አስታወቁ፡፡ባለፉት 3 ቀናት ብቻ 49 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡን ያወሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሚኒስትሮች የፀረ ኮቪድ -19 ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደመቀ መኮንን፤ ይህም በሽታው በአጭር ጊዜ ውስጥ በፍጥነት የመዛመት ዕድል እንዳለው በግልጽ ያመላክታል ብለዋል፡፡ አያይዘውም፤ የወረርሽኙ አዝማሚያ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በመረዳት በወቅታዊ ጉዳዮች ሳንዘናጋ የጥንቃቄ መመሪያዎችን አጥብቀን ተግባራዊ እንድናደርግ ሲሉ አሳስበዋል፡፡ የማህበረሰብ ጤና ባለሙያው ዶ/ር ቴዎድሮስ ታመነ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፤ ሰሞኑን የበሽታውን ስርጭት አስመልክቶ ከሚቀርቡት ሪፖርቶች መረዳት እንደሚቻለው በበሽታው መያዛቸው ከተረጋገጠባቸው ሰዎች መካከል አብዛኞቹ በለይቶ ማቆያ ውስጥ ያልነበሩና በማህበረሰቡ ውስጥ የነበሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ይህ ሁኔታም በሽታው ወደ ማህበረሰቡ ዘልቆ ገብቷል የሚለውን ሥጋት ያጠናክረዋል ያሉት ዶ/ር ቴዎድሮስ፡፡ በበሽታው  መያዛቸው ይፋ ከተደረገባቸው ሰዎች መካከል በድንገተኛ የናሙና ጥናት የተገኙ መኖራቸው ችግሩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል ብለዋል፡፡ በአገራችን የኮቪድ 19 ቅድመ ዝግጅትና ምላሽ ዋና አስተባባሪ አቶ ዘውዱ አሰፋ እንደገለፁት፤ በቅርቡ ቫይረሱ እንዳለባቸው ከተረጋገጠባቸው ሰዎች መካከል አብዛኛዎቹ ምንም አይነት የውጪ ጉዞ ያልነበራቸው፣ በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነትና ንኪኪ የሌላቸው መሆኑና አብዛኛዎቹም በለይቶ ማቆያ ውስጥ ያልነበሩ መሆናቸው የበሽታው ስርጭት ወደ ማህበረሰቡ ውስጥ ገብቶ ይሆናል የሚለውን ጥርጣሬ ማስነሳቱን ጠቁመው፤ ይህንን ሁኔታ ለማረጋገጥ ግን ተጨማሪ ምርመራዎች ሊደረጉ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡ ከለይቶ ማቆያ ውጪ ሆነው ቤት ለቤት በተደረገ አሰሳ በቫይረሱ ተጠርጥረው ተጨማሪ ምርመራ ከተደረገላቸው፣ በጤና ተቋማት ውስጥ ተኝተው ከሚታከሙ ህሙማንና፣ ከፍተኛ ተጋላጭነት አላቸው ተብለው በሚታሰቡ ቦታዎች ላይ በተደረጉ ምርመራዎች፣ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች መገኘታቸውን ያመለከቱት አቶ ዘውዱ፤ ይህም ሁኔታ በሽታው በማህበረሰቡ ውስጥ መግባቱን የሚያመለክት ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም፤ ለበሽታው ከፍተኛ ተጋላጭነት አላቸው ተብለው በሚታሰቡ እንደ አረጋውያን መንከባከቢያ፣ ሕጻናት ማሳደጊያ፣ ማረሚያ ቤቶችና መሰል ተቋማት ላይ የአሰሳ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የህብረተሰብ ጤና ባለሙያዎች በኮቪድ 19 በሽታ መከላከል ኮሚቴ ውስጥ የሚሰሩት ዶ/ር ሰለሞን ወርቁ በበኩላቸው፤ “በለይቶ ማቆያ ውስጥ ከነበሩ ሰዎች ውጪ የሆኑና በህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡ የበሽታው ስርጭት ወደ ማህበረሰቡ ውስጥ ለመግባቱ አመላካች ነው፤ ይህ ደግሞ ጥሩ ዜና አይደለም::ምክንያቱም በሽታው ወደ ማህበረሰቡ ውስጥ ከገባ ለመቆጣጠርና ስርጭቱን ለመከላከል አስቸጋሪ ሁኔታዎች ይፈጠራሉ::” በሽታው ኖሮባቸው እንዳለባቸው የማያውቁ ወይም ምልክት የማያሳዩ ሰዎች ደግሞ በሽታውን በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው ለማስተላለፍ ይችላሉ፤ ይህ ደግሞ አደጋውን የከፋ ያደርገዋል ብለዋል - ዶ/ር ሰለሞን፡፡የበሽታው ስርጭት ፍጥነትና የመሰራጫ መንገዱ ከፍተኛ ጥንቃቄን የሚሻ መሆኑን ያመለከቱት ዶ/ር ሰለሞን፤ ጤናማ መስለው በሽታውን የሚያሰራጩ በርካታ ሰዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርግና ራሱን ከቫይረሱ ሊከላከል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ባለፈው ረቡዕና ሐሙስ በተደረገው ምርመራ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች በሻይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን በተለይ ከትናንት በስቲያ ቫይረሱ ከተገኘባቸው 29 ግለሰቦች መካከል 19ኙ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችና የጉዞ ታሪክ የሌላቸው እንዲሁም በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ ያልነበራቸው መሆናቸው ትልቅ ስጋት ፈጥሯል፡፡ትናንት አርብ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠውን 3 ሰዎች ጨምሮ፣ እስካሁን 194 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን ለ30ሺ 306 ሰዎች ምርመራ መደረጉም ተገልጿል፡፡  ", "passage_id": "901fefaf710226942a664b50727ed914" }, { "passage": "የኮሮና ቫይረስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ግብረ ኃይል በማዋቀር በጥብቅ ክትትል እየተሰራ እንደሚገኝና የከፋ ችግር ቢመጣም ለመቋቋም የሚያስችል ዝግጅት ማድረጋቸውን በድሬዳዋ አስተዳደር የጤና ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ለምለም በዛብህ አስታውቀዋል፡፡በአሁኑ ጊዜ አንድ ዩኒቨርሲቲ እና አምስት ትምህርት ቤቶች ለማቆያ እንዲሁም አንድ ማከሚያ ሆስፒታል ተለይተው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡በሳቢያን ሆስፒታል 104 አልጋዎችን በማዘጋጀትና ለባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት ከሚያዚያ 9/2012 ዓ.ም ጀምሮ የኮቪድ-19 ህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ የተናገሩት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ሲ/ር መስከረም አሰፋ ወደ ሆስፒታሉ ገብተው የነበሩ 6 ታማሚዎች ከቫይረሱ መዳናቸውን ጨምረው ገልፀዋል፡፡መደበኛ የጤና አገልግሎቶችን አስመልክተው ወ/ሮ ለምለም በዛብህ በሰጡት አስተያየት የተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ የሚገመግም ቡድን በማዋቀር በየተቋማቱ ምልከታና ዳሰሳ በማድረግ አስፈላጊ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡በተቋማቱ በቦታ ጥበት ምክንያት ርቀት ያለመጠበቅ ችግርን ለመከላከል ድንኳኖችን በመትከል ጭምር እየተጠቀሙ መሆኑን የቢሮ ኃላፊዋ ተናግረዋል ሲል የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር አስታውቋል፡፡", "passage_id": "395ef3a623775df4cf33779e7440760d" }, { "passage": "ተቋሙ በአሁኑ ጊዜ በአገሪቱ ውስጥ በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከዕለት ዕለት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ በመምጣቱ የባለሙያ ድጋፍና እንክብካቤ የሚሹ ሰዎች ቁጥር \"የህክምና ማዕከላት ማስተናገድ ከሚችሉት አቅም በላይ\" እየሆነ መምጣቱን ጨምሮ ገልጿል።\n\nበዚህም ሳቢያ በኮሮናቫይረስ በጽኑ ታምመው በህክምና ተቋማት ድጋፍ ለማግኘት ለሚመጡ ህሙማን አገልግሎት የሚውሉ \"የሰው ሰራሽ የመተንፈሻ መሳሪያ (ቬንትሌተር) እና የኦክስጅን እጥረት እያጋጠመ ነው\" ሲል ገልጿል። \n\nበኢትዮጵያ እስከ ትናንት እሁድ ድረስ በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 175,467 ሰዎች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ፣ 2,550 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው አልፏል።\n\nየኮሮናቫይረስ የመተንፈሻ አካላትን በተለይም ሳንባን የሚያጠቃ ሲሆን በበሽታው ክፉኛ ለተጠቁ ጽኑ ህሙማን ሰው ሰራሽ የመተንፈሻ መርጃ (ቬንትሌተር) እና ኦክስጂን ህይወታቸውን ለመታደግ ለሚደረገው ጥረት በእጅጉ አስፈላጊ ናቸው።\n\nበኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ በጽኑ የታመሙ ሰዎችን ህይወት ለመታደግ በአሁኑ ወቅት በአገልግሎት ላይ የሚገኙት የሰው ሰራሽ የመተንፈሻ መርጃ ቬንትሌተሮች ቁጥር ከ500 ብዙም የበለጠ አይደለም። \n\nስለዚህም በበሽታው የሚያዙት ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩ የህክምና ድጋፍ የሚፈልጉ ሰዎችን መጠን በመጨመር በህክምና ተቋማቱ ላይና በባለሙያዎች ላይ ጫናን በመፍጠር ከአቅም በላይ ሊሆን እንደሚችል ተሰግቷል። \n\nበተለይም በወረርሽኙ በጽኑ ታምመው የቬንትሌተርና የኦክስጂን ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ህሙማን ቁጥር እየጨመረ በመሆኑ የነፍስ አድን አገልግሎቱን መስጠት ከማይቻልበት ደረጃ ላይ ከደረሰ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ሊያሻቅብ ይችላል። \n\nበአሁኑ ወቅት በመላው አገሪቱ በየዕለቱ የሚመዘገበው በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የገለጸው ኢንስቲትዩቱ፤ ከዚሁ ጋር ተያይዞም በወረርሽኙ ሳቢያ የጽኑ ህሙማን የህክምና አገልግሎት የሚፈልጉ ህሙማንና ህይወታቸውን የሚያጡ ሰዎች ቁጥር \"አስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል\" ይገኛል ብሏል።\n\nየኮሮናቫይረስ በኢትዮጵያ ውስጥ መገኘቱ ይፋ ከተደረገ ባለፈው ቅዳሜ አንድ ዓመት የሞላው ሲሆን፣ በዚህ ጊዜ እስካሁን ድረስ በወረርሽኙ ሳቢያ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 2550 ደርሷል።\n\nበኮቪድ-19 ለሞት ከተዳረጉት ሰዎች መካከል 74 በመቶ የሚሆኑት በህክምና ማዕከላት ውስጥ ሲሆን 24 በመቶዎቹ ደግሞ በአስክሬን ላይ ከተወሰደ ናሙና ላይ በተደረገ ምርመራ የተገኘ መሆኑ ተገልጿል።\n\nኢንስቲቲዩቱ እንደሚለው ባለፉት ጥቂት ቀናት እየተመዘገበ ያለው የሟቾች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ነው።\n\nእስካሁን ድረስ በየዕለቱ ከተመዘገቡት ሞቶች ሁሉ ከፍተኛው በእነዚህ ቀናት ውስጥ ተመዝግቧል። \n\nበወረርሽኙ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር በተለያዩ የአገሪቱ ከፍሎች የተመዘገቡ ሲሆን በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ውስጥ የተመዘገበው የሟቾች ቁጥር ከሌሎቹ ቦታዎች አንጻር በእጅጉ ከፍተኛ ነው። \n\nበዚህም መሠረት በአዲስ አበባ 1,852 ሰዎች በኮቪድ-19 ሳቢያ ለህልፈት ሲዳረጉ ይህም ከአጠቃላዩ የሟቾች ቁጥር 73 በመቶውን ይይዛል።\n\nበተከታይነት በኦሮሚያ ክልል 256 ሰዎች (10 በመቶ)፣ በአማራ ክልል 105 ሰዎች (4 በመቶ)፣ በሲዳማ ክልል 75 ሰዎች (3 በመቶ) የሚሆኑት በበሸውታው ህይወታቸው አልፏል። \n\nበየዕለቱ በሚደረገው ምርመራ ቫይረሱ የሚገኝባቸው ሰዎች ቁጥርም በፍጥነት እየጨመረ መሆኑ ተገልጿል። \n\nቬንትሌተር ምንድን ነው?\n\nቬንትሌተር የሰውነታችንን የአተነፋፈስ ሥርዓት ተክቶ የሚሠራ ማሽን ነው። የህሙማን ሳምባ እክል ሲገጥመው ቬንትሌተር የመተንፈስ ተግባር ስለሚያከናውን ህይወትን ይታደጋል። ... ", "passage_id": "bff31931d440e913e8d49fb4a6700a1e" }, { "passage": "በድንበር አካባቢ ያሉ ለይቶ ማቆያዎችን ለማጠናከር ጥረት እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ለቪኦኤ አስታውቀዋል።በመላ ሃገሪቱ፤ በዋናነት አዲስ አበባ ውስጥና በድንበር አካባቢዎች በሚገኙ 170 ለይቶ ማቆያዎች ውስጥ ከሰባ ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሚገኙ የተናገሩት ዶክተር ደረጀ የተጣበቡ ለይቶ ማቆያዎችን ለማስፋት የሚያስችል ድጋፍ ከዓለም ባንክ መገኘቱን ገልፀዋል።በደወሌ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለውን መጨናነቅ ለመቀነስም ከዩኒሴፍ የተገኙ 4 ድንኳኖችን አራርቆ በመትከል ሥራ ለማስጀመር ዕቅድ እንዳለ ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል።\n", "passage_id": "4b5e3880a4113b17085fe642ee6e93c9" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) ኬንያ በኮሮና ቫይረስ ተይዘው የቫይረሱን ምልክት ያላሳዩ ህመምተኞችን ከሆስፒታሉ ልታስወጣ መሆኑን ገልጻለች ።የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊ ራሺድ አማን ÷በአገሪቱ በኮሮና ቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ ሁሉንም ታማሚዎች በሆስፒታሎች ውስጥ ማከም ከባድ ስለሆነ ውሳኔውን መተላለፉን ተናግረዋል።በዚህም በቫይረሱ የጤናቸው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ያልደረሰና እና በቤታቸው ውስጥ ክትትል ማድረግ የሚችሉበት ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ታማሚዎች ከሆስፒታሉ በመውጣት በቤታቸው መቆየት እንደሚችሉ ተነግሯል ።መንግሥት ታማሚዎቹ ከሆስፒታል የሚወጡበትን መመሪያ ማዘጋጀቱም ነው የተገለጸው።በዚህም ታማሚዎቹ በቤታቸው ቢያንስ ለአስር ቀናት እራሳቸውን በመለየት የሚቆዩ ሲሆን ውሳኔውን ለማስፈጸምና ታማሚዎቹን ለመከታተል በማህበረሰብ ጤና ሰራተኞች የቤት ለቤት ክትትል እንደሚደረግላቸውም አስታውቋል፡፡በምስራቃዊቷ ሃገር እስካሁን 3ሺህ 94 ሰዎች በኮሮናቫይረስ ተይዘዋል።ምንጭ፡-ቢቢሲ", "passage_id": "bdc6b9d9c60fb606f28090de1dff8a4d" } ]
6cbdfad4a3dc4b144811385eb9987d79
beee7e7893145ec105cd6cb0ad309985
ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን ሳተላይት አመጠቀች
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን ሳተላይት ማምጠቋን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ትናንት የመጠቀችው የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሳተላይት በሰላም መምጠቋን ገልጿል፡፡ኢንስቲትዩቱ እንዳመለከተው ኢትዮጵያ አሁን ያመጠቀቻት ሳተላይት ET-Smart-RSS የምትባል ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ETRSS-1 የተባለች የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታኅሣሥ ወር 2012 ዓ.ም ማምጠቋ ይታወሳል።አምና የመጠቀችው ይህች ሳተላይትም መረጃ መላክ የጀመረች ሲሆን፤ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናት እና ምርምሮችን ለመሥራት እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደምትገኝም ነው መረጃዎች የሚያሳዩት፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37920
[ { "passage": "\"ለኢትዮጵያ ሳተላይት ማምጠቅ ቅንጦት አይደለም\" የኢትዮጵያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር\\nየመሬት ምልከታ ሳተላይት መሬትን እየቃኘ መረጃዎችን በፎቶ ይመዘግባል\n\nሳተላይቱ ከምድር ወደ ህዋ ከተመነጠቀ በኋላ መሬትን እየቃኘ መረጃዎችን በፎቶ ይመዘግባል። እንደያስፈላጊነቱም መረጃውን ወደ ምድር ይልካል።\n\nአፍሪካ ውስጥ እስካሁን ሳተላይቱን ያመጠቁ በጣት የሚቆጠሩ ሀገሮች ናቸው። ኢትዮጵያም የአምጣቂዎቹን ቡድን ለመቀላቀል መሰናዶ የጀመረችው ከሁለት ዓመት በፊት ነበር።\n\nሳተላይቱን ሀገር ውስጥ ለመስራት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ለማምጠቅ የሚያስፈልገው ቴክኖሎጂና የሰው ሀይል ባለመኖሩ ወደ ሩቅ ምሥራቅ ስታማትር፤ ቻይና የገንዘብና የሙያም እገዛ ለመስጠት ተስማማች።\n\n• ኦነግ እና መንግሥትን ለማግባባት የሃገር ሽማግሌዎች እየጣሩ ነው\n\n• ትራምፕ ጠቅላይ አቃቢ ሕጉን አባረሩ \n\nከቻይና 6 ሚሊየን ዶላር ተለግሶ ስራው ተጀመረ። ቻይናውያን ኢንጂነሮች ኢዮጵያውያንን እያሰለጠኑ ሳተላይቱ ቻይና ውስጥ እንዲሁም በከፊል ኢትዮጵያ ውስጥ ተገነባ።\n\n70 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ሳተላይት በ2012 ዓ. ም. መባቻ ላይ ከቻይና ይመጥቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሰለሞን በላይ ለቢቢሲ ተናግረዋል።\n\nሳተላይቱ በቻይና እገዛ ከምድረ ቻይና ይምጠቅ እንጂ፤ \"ተቆጣጣሪዋም፣ አዛዧም ኢትዮጵያ ናት\" የሚለውን አስምረውበታል።\n\nሳተላይት ማምጠቅ ለምን አስፈለገ?\n\nየህዋ ጥናት በዓለም ላይ በፍጥነት እየዘመኑ ካሉ ዘርፎች መካከል ይጠቀሳል። የሰው ልጅ ምድር ጠባው አልያም ከምንኖርበት ዓለም ውጪ ያለውን ለማወቅ ጓጉቶ ዘወትር እየቆፈረ ነው።\n\nከህዋ ፍተሻ በተጨማሪ ህዋን ተጠቅሞ መሬትን ማሰስ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ተግባር ነው። ሳተላይቱ መረጃ ሲሰበስብ ይህ ቀረህ አይባለውም። ከግዙፍ ክንውኖች እስከ ጥቃቅን እንቅስቃሴዎች ይመዘግባል።\n\nእንደ ባለሙያዎች አባባል ሳተላይቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው። የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ የተፈጥሮ አደጋዎች ከመድረሳቸው አስቀድሞ ለመተንበይ፣ ደህንነትን ለመጠበቅ ወዘተርፈ ይውላል።\n\nበእርግጥ ብዙዎች በታዳጊ ሀገር የህዋ ጥናት አስፈላጊነቱ ላይ ጥያቄ ቢያነሱም፤ ዶ/ር ሰለሞን \"ህዋ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገሮች የመኖርና ያለመኖር ጥያቄ ነው፤ ቅንጦት አይደለም\" ይላሉ።\n\nየአየር ንብረት ለውጥ የመላው ዓለም ስጋት በሆነበት ዘመን፤ አንዳች ተፈጥሯዊ አደጋ ከመድረሱ በፊት አስቀድሞ መረጃ ማግኘት ብልህነት ነው።\n\nየዛፍ ቁጥር፣ የአየር ንብረት ለውጥና ሌሎችም መረጃዎች ከተሰበቡ በኋላ እንደ ጎርፍ ያሉ አደጋዎች ከመከሰታቸው በፊት መተንበይ ይቻላል።\n\n• ግጭትን ለማባባስ ፌስቡክ ጥቅም ላይ ውሏል ተባለ \n\n• በቤታችን ውስጥ ያለ አየር የጤናችን ጠንቅ እንዳይሆን ማድረግ ያለብን ነገሮች \n\nግብርና ቀዳሚ መተዳደሪያ በሆነባት ሀገር የቱ አካባቢ ምርታማ ነው? የአየር ንብረት ለውጥ ይኖር ይሆን? የሚሉ ጥያቄዎች በቀላሉ እንዲመለሱ የሳተላይቱ መረጃ አስፈላጊ ይሆናል።\n\nዶ/ር ሰለሞን እንደሚሉት፤ አንድ የግብርና አካባቢን የሚያሳይ ፎቶግራፍ ስለ እርሻ መሬቱ፣ ስለ ውሀው፣ ስለ አፈሩ ዝርዘር መረጃ ይሰጣል። መረጃዎቹን በመጠቀም ምርታማ የሆኑ አካባቢዎችን መለየት፣ የምርት መጠንን በትክክል ማወቅም ይቻላል።\n\nኢንዱስትሪዎች እየተስፋፉ በመጡባት ኢትዮጵያ፤ ፋብሪካዎች የት መገንባት አለባቸው? ለሚለው ጥያቄ የሳተላይቱ መረጃ መልስ ሊሰጥ ይችላል።\n\nሕዝብ መቁጠር ሲያስፈልግ ከዘልማዳዊው መንገድ ሳተላይቱን መጠቀም ይመረጣል። ትክክለኛ መረጃ ከማግኘት፣ ገንዘብና የሰው ሀይል ከማዳን አንጻርም የተሻለው አማራጭ ነው።\n\nሳተላይቱን ደህንነትን ከመጠበቅ ጋር የሚያስተሳስሩት ባለሙያዎች አሉ። ዶ/ር ሰለሞን በበኩላቸው \"በመርህ ደረጃ ህዋ የሚውለው...", "passage_id": "5678c023801c702ac33c8aa2569abd23" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ ሰኔ 08/2012 ዓ.ም (አብመድ) ሳተላይቷ በሚሰጣት ትዕዛዝ መሠረት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ ክትትል በማድረግ መረጃ እንደምታደርስ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬተር ሰሎሞን በላይ (ዶክተር) ለአብመድ ተናግረዋል፡፡ሁለተኛውን የዓለም ጦርነትን ተከትሎ የፉክክር መድረክ መሆን የጀመረው የሕዋ ምርምር አሁንም የሀገራት የቴክኖሎጂ ደረጃ መመዘኛ እንደሆነ ቀጥሏል፡፡ ኢትዮጵያም ከብዙ መዘግዬት በኋላ ዘርፉን ተቀላቅላለች፤ ለዘርፉ ተወዳዳሪነትም ሌት ተቀን እየተጋች ነው፡፡ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ደግሞ ይህንን ዘርፍ እየመራ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደሕዋ ያመጠቀቻት ሳተላይት በስኬት ሥራዋን ዶክተር ሰሎሞን ስለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሲያስረዱም ግድቡ የዛሬ ብቻ ሳይሆን የነገ ኢትዮጵያውያን ጭምር በመሆኑ ‘‘የጉባው የኃይል ማመንጫ ነጭ የደም ሕዋስ ነው’’ ብለዋል፡፡ ለሳተላይቷ ትዕዛዝ በመስጠት ግድቡን በሚመለከት መረጃ አንድትልክ እየተደረገ ስለመሆኑም አብራርተዋል፡፡ ስለግድቡም ሆነ ስለሚፈለገው ማንኛውም መረጃ ሳተላይቷን በማዘዝ መረጃ እየተሰበሰበ እንደሆነና የግድቡን ደኅንነት በሚመለከትም አስፈላጊውን መረጃ ተቋሙ እየተቀበለ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡በቅርቡ የኮሙዩንኬሽን ሳተላይት የማምጠቅ ዕቅድ ያለው ተቋሙ በ15 ዓመት ውስጥ ቢያንስ 10 ሳተላይቶቸን ወደሕዋ ለማምጠቅ ዕቅድ ይዟል፡፡ በአፍሪካ ካሉ የሕዋ ምርምር ተቋማት ውስጥ ተወዳዳሪ መሆን የቻለው ኢንስቲትዩቱ ዘርፉን የሚመራ ፖሊሲ እና ስትራቴጅም ማጽደቁን አስታውቋል፡፡የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ወደፊት ቀጣይ የሀገሪቱ መመኪያ ይሆን ዘንድ በሀገር ውስጥ እና በውጭ የተለያዩ ተመራማሪዎችን በማሰልጠን ላይ ነው፡፡ዘጋቢ፡- አንዷለም መናን", "passage_id": "b91294f77eea1ceb00beabac94bb5585" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ በ2012 መጀመሪያ ወራት ሳተላይቷን ወደ ኅዋ እንደምትልክ ተገለጸ።  የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሩያ እንዳሉት  የሳተላይት ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ በመሆኑ  ኢትዮጵያ  በ2012 መጀመሪያ ወራት የራሷን  ሳተለይት ወደ ህዋ ታመጥቃለች። ሚኒስትሩ ዛሬ  ሚያዚያ 1 ቀን 2011 ዓም  የሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸውን የአንድ ዓመት አፈጻጸም አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከቻይና ስፔስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር እየገነባ ያለው  ሳተላይት በመጠናቀቅ ላይ በመሆኑ በቀጣዩ ዓመት የመጀመሪያዎቹ  ወራት  ኢትዮጵያ የራሷን  ሳተላይት  ወደ ኅዋ  እንደምታመጥቅ ገልጸዋል፡፡ሚኒስትሩ\n እንዳሉት ሳተላይቷ ለግብርና፣ ለውሃ፣ ለአከባቢ ጥበቃ፣ ለማዕድን\nልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ ክትትል አገልግሎት የሚውል መረጃዎችን የምታሰባሰብ  ናት።  ሳተላይቷ  71ኪሎ ግራም የምትመዝን ስትሆን  አስር ዓመታትን በኅዋ ላይ የመቆየት አቅም እንደሚኖራትም  ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በቀጣይ  በራሱ አቅም ሳተላይቶችን መገንባት የሚያስችለው  የሳተላይት ፋብሪካ፣ መገጣጠሚያና መፈተሻ ማዕከል ለመገንባት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኝም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡ አሁን ላይ ተጨማሪ የሳተላይት መረጃ መቀበያ መሠረተ ልማትም  በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኝም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። አዲሱ ገረመው", "passage_id": "c46860242c954b22311bd30b0e3c0e78" }, { "passage": "ኢትዮጵያ በታሪክ የመጀመሪያዋ የሆነችውን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ወደ ሕዋ ለመላክ በታኅሳስ 7/2012 መርሃ ግብር ተይዞለት የነበረ ቢሆንም በሦስት ቀናት እንዲገፋ መደረጉ ታወቀ። ሳተላይቷ ከቻይና የምርምር ጣቢያ ወደ ሕዋ የምትመጥቅ ሲሆን፤ በከተማው ያለው የአየር ሁኔታ ሳተላይቷን ወደ ሕዋ ለማስወንጨፍ አስቸጋሪ በመሆኑ በሦስ ቀናት ተራዝሞ ታኅሳስ 10/2012 እንዲሆን መደረጉን የኢፌዲሪ የሳይንስና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር አስታውቋል።ETRSS-1 የተሰኘችው የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ወደ ሕዋ በመጓዝ በርካታ መረጃዎችን ወደ ምድር እንደምትልክ የታመነባት ሲሆን፤ በተለይም ደግሞ ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚኖረው መረጃ ወደ ምድር እንደምትልክ ታውቋል።ከሳተላይት ማምጠቁ ጋር ተያይዞም ኢትዮጵያ የሳተላይት መቆጣጠሪያ እና መረጃ መቀበያ ጣቢያ በእንጦጦ ኦብዘረቫቶሪና ምርምር ማዕከል ውስጥ በመገንባት ላይ የምትገኝ ሲሆን፤ የሳተላይት መረጃ መቀበያ አንቴና ግንባታውም በቅር መጠናቀቁ ይታወሳል።", "passage_id": "66c26b48df7ab244f1e42d1dfcf3c4b8" }, { "passage": "ኢትዮጵያ የሳተላይት መቆጣጠሪያ እና መረጃ መቀበያ ጣቢያ በእንጦጦ ኦብዘረቫቶሪና ምርምር ማዕከል ውስጥ እየገነባች ሲሆን የመሬት ምልከታ ሳተላይት መቀበያ አንቴናም ዛሬ ኅዳር 19/2012 ተገንብቶ ተጠናቋል። የኢትዮጵያ የህዋ ሳይንስ ቴክሎጂ ኢኒስቲቲዩት እንዳስታወቀውተገንብቶ የተጠናቀቀው ሳተላይት መረጃ መቀበያ አንቴና በመጪው ወር ታኅሳስ 1/2012 ወደ ህዋ ኢትዮጵያ የምታመጥቀውን ሳተላይት መረጃ ለመቀበል እንደሚረዳ አስረድቷል። ጣቢያው መረጃዎችን ከመቀበል ባለፈ ሳተላይቶች በአግባቡ ተልዕኳቸውን መፈፀማቸውን ክትትል የሚደረግበት፣ የሳተላይቶች ደህንነትና እንቅስቃሴንም ቁጥጥር የሚደረግበት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የእንጦጦ የሳተላይት መቆጣጠሪያ እና መረጃ መቀበያ ጣቢያ ፕሮጀክት ከተለያዩ ሳተላይቶች መረጃ መቀበል የሚያሥችል አንቴናና መረጃዎች የሚተነተኑበት የመረጃ ማዕከል ግንባታም እያከናወነ ይገኛል፡፡\nኢትዮጵያ የሳተላይት መረጃ ፍላጎቷን በከፍተኛ ወጪ የምታገኝ ሲሆን ፤ ይህንን በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለግዢ የሚወጣ የአገር ሃብት ለማዳን ያስችላል፡፡የጣቢያው መገንባት በአገር ውስጥና በአጎራባች አገራት ለሚገኙ የሳተላይት መረጃ ተጠቃሚዎች የመረጃ አገልግሎቱን በመሸጥ ገቢ ማስገኘትም እንደሚያስችል ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል፡፡", "passage_id": "151b96808a88d8562cb67b7ee0c113ad" } ]
109196fbfd295548867bb670973d7285
b699c0f168a68d173ffcc659dfaf81a2
ብልህ ከታናሹ ይማራል
 የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በእድሜም፣ በስምም፣ በተቋም ግዝፈትም ታላቅ ስለመሆኑ የሚጠራጠር አይኖርም።እነዚህ ታላቅና ታናሽ ተቋማት አሁን ያሉበት ቁመናና ተግባር ከእግር ኳሱ ጥቅም አኳያ እንደሚለያይ ብዙ ማሳያዎችን ማስቀመጥ ይቻላል።በተለይም እግር ኳሱን በዘመናዊ መንገድ ከመምራት አንፃር ታናሹ የተሻለ ስኬት እስመዘገበ በጥሩ ጎዳና ሲጓዝ ታላቁ ወደ ኋላ እየቀረ መምጣቱን በማስረጃዎች መከራከር የሚቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል።ብልህ ከታናሹ ይማራልና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዘንድሮው የከተማዋ ዋንጫ ካሳካቸው ቁም ነገሮች ጥቂቶቹን እንኳን መማር ከቻለ ብዙ ነገር መለወጥ እንደሚችል ይታመናል። በእነ ኢንጂነር ሃይለእየሱስ ፍስሃ የሚመራው የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ ባይሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ ለእግር ኳሱ የሚበጁና መደረግ ያለባቸውን ተግባራት በመፈፀም ላይ ይገኛል። ከጥቅምት 20 እስከ ህዳር 14/2012 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ስታድየም ሲካሄድ የነበረውን የአዲስ አበባ ዋንጫ ውድድርን መነሻ በማድረግ፤ በውድድሩ ተሳታፊ ለነበሩት ብቻ ሳይሆን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለስፖርቱ እድገት አስተዋፅኦ አላቸው ላሏቸው ግለሰቦችና ተቋማት ምስጋናና እውቅና ሰጥቷል። በዚህም መሰረት ለክለቦች ከ150,000 ብር እስከ 752,000 ብር ድረስ እንደየደረጃቸው ሸልሟል።ለግለሰቦች ደግሞ ከ10,000 ብር እስከ 75,000 ብር ወጪ በማድረግ በድምሩ 2 ሚሊዮን ብር አካባቢ አበርክቷል። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንኳን ዓመቱን ሙሉ በሚያከናውናቸው ውድድሮች በታሪክ አሳክቶት የማያውቀውን የሽልማት መጠን በማሳካት ክለቦች የሚመጥናቸውን ክብር በመስጠቱ አለማድነቅ አይቻልም።በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚሳተፉ ክለቦች ለተጫዋቾች ዝውውር ፣ ደሞዝ፣ ትራንስፖርትና ሌሎች ወጪዎች በዓመት በአማካይ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ያወጣሉ። በፕሪሚየር ሊጉ ሚሊዮኖችን ወጪ አድርገው ተሳትፈው የሚያገኙት አንዳች ነገር አለመኖሩ ግን አስገራሚ ነው።ዓመቱን ሙሉ ውድድር አድርጎ የፕሪሚየር ሊጉ ቻምፒዮን የሚሆን ክለብ 150 ሺህ ብር ይበረከትለታል። ይህ ደግሞ በአስር ቀን ውድድር ብቻ ከ750 ሺ ብር በላይ ሽልማት ከሚያስገኘው የአዲስ አበባ ዋንጫ አንፃር ምንም ነው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ዘንድሮ የአዲስ አበባ ዋንጫን በማንሳቱ ይህን ሽልማት ወስዷል።በፕሪሚየር ሊጉ ይህን ያህል የገንዘብ ሽልማት ለማግኘት ግን በተከታታይ አምስት ዓመታት ቻምፒዮን መሆን ይጠበቅበታል።ፕሪሚየር ሊጉን የሚያሸንፍ ክለብ 150 ሺህ ብር የሚሸለም ሲሆን፤ የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለአዲስ አበባ ዋንጫ ለተሳትፎ ብቻ 150 ሺህ ብር የመጨረሻው ሽልማቱ ነው። ከዚህ በመነሳት ብሄራዊ ፌዴሬሽኑም ሆነ አዲሱ ሊጉን የሚመራው ዓብይ ኮሚቴ ከአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሽልማት አሰጣጥ አንድ ነገር መማር እንዳለበት ብዙዎች ይስማማሉ። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ታህሳስ 14 ቀን 2012 ዓ.ም በኢንተርኮንቴኔንታል ሆቴል ባዘጋጀው መድረክ እውቅና ከሰጣቸው ተቋማት አንዱ ዳሸን ባንክ ነበር። ባንኩ በአሞሌ አማካኝነት ተመልካቾች ሳይጉላሉ በየቤታቸው ሆነው ትኬት ቆርጠው ስቴድየም እንዲገቡ በማድረግ ላበረከተው አስተዋጽኦ ሽልማቱ ሊበረከትለት ችሏል። ከዚህ ሁነት በመነሳት ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ልምድ ሊወስድ የሚገባው የትኬት አሻሻጥ ሥርዓት እንዳለ መረዳት ይቻላል።የተመልካቾች ስታዲየም መግቢያ ቲኬት ሲሸጥ የነበረው በዳሸን አሞሌ አማካይነት የኦን ላይን የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ነበር። በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚስተዋሉ ረዣዥም ሠልፎችን ያስቀረ ከመሆኑ ባሻገር፣ የተጭበረበሩ (ፎርጅድ) ትኬቶች ሥራ ላይ እንዳይውሉ ያስቻለ ቴክኖሎጂ ነው። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ለ22 ዓመታት ከተጓዘበት መንገድ ለመውጣት የሚያስችል ቴክኖሎጂን ተግባራዊ ለማድረግ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቶ ወደ ተግባር ሳይለውጥ መቆየቱን በማስታወስ፤ ከመዲናዋ እግር ኳስ መማር እንደሚገባውም የስፖርት ቤተሰቡ ያምናል። መስከረም 25 ቀን 2010 ዓ.ም ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በአዲስ አበባ ስታዲየም የመግቢያ ትኬት ለመቁረጥ የሚፈጠረውን ረጅም ሰልፍ የሚያስቀር ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ሊያውል እንደሆነ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። የፌዴሬሽኑ የማርኬቲንግ ዳይሬክተር አቶ ኢሳያስ ታፈሰ በጊዜው ቴክኖሎጂው ለዚሁ ስራ በሚከፈቱ ጣቢያዎች፣ በሞባይልና በኢንተርኔት አማካኝነት ጥቅም ላይ እንደሚውል ነበር የተናገሩት። የኢ-ቲኬት ሽያጭ አሰራሩን ተግባራዊ ለማድረግ ክፍያ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ከተሰኘ ተቋም ጋር ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። የኢ-ትኬት አገልግሎት ሽያጭ ከሚያዚያ 25 ቀን 2010 ዓ .ም ጀምሮ አገልግሎቱ በይፋ እንደሚጀመር ተነግሮ የነበረ ቢሆንም፤ የተባለው መሬት ላይ ወርዶ አልታየም። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለመገናኛ ብዙሃንና ለስፖርት ጋዜጠኞች እውቅናና ሽልማት ማበርከቱ ሌላ የሚያስመሰግነው ተግባር ነው።ይህ ተግባር በተለይ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ዝቅ ብሎ ሊቀስመው የሚገባ መልካም ተግባር እንደሆነ በብዙዎች ተነግሯል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ለመገናኛ ብዙሃን በሩን ክፍት አድርጎ መረጃን እንደማይሰጥ በተደጋጋሚ ቅሬታ የሚሰማበት መሆኑና ፤ ጋዜጠኞችን በሚሰሩት ሥራ በማበረታታት በአብሮነት ከመስራት ይልቅ በሩን ዝግ አድርጎ የሚሰራ መሆኑ ዘወትር ሲያስወቅሰው ይሰማል። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውድድሩን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ሲያስተላልፍ የነበረውን የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክን ልዩ ተሸላሚ ያደረገ ሲሆን ፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ውድድሮችን በቀጥታ በማስተላለፍ ለህዝብ ተደራሽ ወደ ማድረግ አሰራር መግባት እንደሚገባው ልምድን መቅሰም እንዳለበት ያሳየ አጋጣሚ ነው።ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ከሶስትና አራት ዓመት በፊት በፕሪሚየር ሊጉ የተመረጡ ጨዋታዎችን በቴሌቭዥን የቀጥታ ስርጭት ለማስተላለፍ ስምምነት ላይ ደርሶ ነበር። በፕሪሚየር ሊጉ የሚደረጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ማግኘት ተከትሎ ለፌዴሬሽኑም ሆነ ለክለቦች ከስፖንሰር ሺፕ ከፍተኛ የሆነ ገቢ ማግኘት የሚቻልበት አጋጣሚ ግን እስካሁን ተግባራዊ አልሆነም። አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 23/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=25048
[ { "passage": "‹‹ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እጅግ ዘግናኝ የሆነ ችግር እያስከተለብን ነው።እኔ የተሰማራሁበት የሥራ ዘርፍ ከቀን ሰራተኛ እስከ ከፍተኛው ድረስ ያካተተ ነው። በሽታው በቀን ሰርቶ የዕለት ጉርሱን የሚሸፍነውን ከሥራ ውጭ እያደረገው ነው። ለዚህ የህብረተሰብ ክፍል እንደ አደጉት ሀገራት ሌሎች አማራጮችን ማስቀመጥ አንችልም። የችግሩ ስፋት በዚህ ልክ ነው የሚገለጸው›› በማለት በሽታው ችላ ሊባል እንደማይገባው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ይገልጻል፡፡ አትሌት ኃይሌ፤ በሽታው አሳሳቢ ቢሆንም ጭራቅ አድርጎ መሳልም የተሳሳተ እንደሆነ ይናገራል። በሀኪሞች የሚሰጠውን ምክር ተግባራዊ በማድረግ እራስን በመጠበቅ ሌሎችንም መታደግ ይገባል ሲል ይመክራል። አንድ ሰው ጉንፋን ሲይዘው ወደ ሌላ እንዳያስተላልፍ እንደሚጠነቀቀው ሁሉ ይህም ወረርሽኝ እስኪገታ መጠንቀቁ እንደሚበጅ ይናገራል። ምንም እንኳን ወረርሽኙ በየንክኪው ንጽህና መጠበቅን የሚያስገድድ ቢሆንም የግል ንጽህናን መጠበቅ በእጅ አማካኝነት ከሚተላለፉ በሽታዎች ይከላከላል ብሎ ያምናል። በግሉም በሀኪም የተሰጡ የቅድመ ጥንቃቄ የእጅ ንጽህና መጠበቂያዎችን በመጠቀም ጥንቃቄውን ጨምሯል። መጨባበጥም አቁሟል። ‹‹ይተላለፍብኛል ብቻ ሳይሆን አስተላልፋለሁ ብሎ ማሰብም ይገባል›› ይላል፡፡ኃይሌ ከእርሱም አልፎ የድርጅቱ ሰራተኞችና ደንበኞቹ ለበሽታው እንዳይጋለጡ ጥንቃቄው እስከነርሱ ዘልቋል። ስጋቱ ኢኮኖሚው ላይ ተጽዕኖ አሳድሮ ህዝብን ለረሃብ አደጋ እንዳያጋልጥ መጠንቀቅ ላይም መዘናጋት መኖር የለበትም ብሏል፡፡በዚህ አጋጣሚ የዋጋ ንረት ያስከተሉትንና አላስፈላጊ ሸመታ ያካሄዱትንም ኮንኗል። በዚህ ጊዜ የግል ጥቅም የሚታሰብበት እንዳልሆነ ይገልጻል። ኪሳራ ቢደርስም የግለሰብ ሳይሆን የሀገር መሆኑን መገንዘብ እንደሚገባ ያስረዳል። ሁሉም እኩል የሚጨነቅበት ወቅት መሆኑን በመጠቆም፣ እርሱ ለግሉ ብቻ ሳይሆን በሥሩ ላሉ ሶስት ሺ ሶስት መቶ ሰራተኞቹ ጭምር እንደሚጨነቅ ነው የተናገረው። ጥንቃቄው ከቤት ጀምሮ ከተተገበረ ውጤት ይመጣል ብሎ ያምናል፡፡ብዛት ያለው ሸማች ከሚያስተናግዱ ተቋማት መካከል የሸማቾች ህብረት ሥራ ማህበራት ይጠቀሳሉ። የህዝብ እንቅስቃሴን ለመቀነስ መንግሥት አብዛኛው ሰራተኛ በቤቱ እንዲቆይ ውሳኔ ቢያሳልፍም ማህበራቱ የዕለት ፍጆታ የሚያቀርቡ በመሆናቸው ሥራቸውን አላቋረጡም። በሽታውን እንዴት እየተከላከሉ ነው የሚለውን ለመቃኘት በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ እፎይታ ሸማቾች ማህበር ተገኝተናል። በበሩ መግቢያ ባዘጋጁት የእጅ መታጠቢያ ሸማቹ ታጥቦ እንዲገባ የመጀመሪያ ጥንቃቄ አድርገዋል። ወረፋ ሲጠብቁ ደግሞ ተጠጋግተው እንዳይቆሙ በተወሰነ ርቀት በእንጨት ችካል አድርገዋል።በተጨማሪም ወረፋውን የሚያስተናብሩት እያስጠነቀቁ መጠጋጋትን ለማስቀረት ጥረት ሲያደርጉ ታዝበናል።ግንዛቤው ገና ቢሆንም ጥንቃቄው ይበል የሚያስብል ነው፡፡የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌትነት መንግሥቱና የማህበሩ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ፀጋው በየበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ሸማቹ ዋጋ ባናሩ ነጋዴዎች እንዳይበዘበዝ የህዝብ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ሲሉ በሥራ ገበታቸው ላይ ተገኝተዋል። \nህዝቡንም ሲያገለግሉ የእራሳቸውንም የሸማቹንም ጤና እየጠበቁ መሆን እንዳለበት በመገንዘብ አስፈላጊውን የቅድመ ጥንቃቄ ተግባር በማከናወን ሥራቸውን በመፈጸም ላይ እንደሆኑ ይገልጻሉ።ይሁን እንጂ ወደ እነርሱ የሚሄደው ሸማች ጉትጎታ መፈለጉ አስቸጋሪ እንደሆነባቸው አልሸሸጉም፡፡አቶ ጌትነት እንዳሉት ሥራቸው በፖሊስ ኃይል ቢታገዝ ሸማቹ ጥንቃቄውን በተሻለ ይተገብራል ብለው ያምናሉ። ሰራተኞቻቸው በየክፍላቸው ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የእጅ ንጽህና መጠበቂያ በመስጠት ጥረት መደረጉንም አመልክተዋል፡፡አቶ ጌትነትም የመከላከያ መንገዶችን በመተግበር እንጂ በመደናገጥና ቸልተኛ በመሆን በሽታውን መከላከል እንደማይቻል ተገንዝቦ የራስን ጥረት ማድረግ እንደሚገባ መክረዋል፡፡ሸማቹን በእጅ ማስታጠብ እንዲያግዙ የወረዳ ዘጠኝ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤትም ትብብር ሲያደርግ አስተውለናል። የጽህፈት ቤቱ ባለሙያ የሆኑት አቶ አወቀ ተስፋ እንደገለጹልን፤ ወጣቱን በማስተባበር በአቅሙ የሚችለውን እንዲያደርግ በጽህፈት ቤታቸው በኩል ጥረት በመደረግ ላይ ነው፡፡ወጣቱ በበጎ ተግባር ሙሉ ፈቃደኛ እንደሆነ የሚናገሩት አቶ አወቀ፣ ሌሎችን ሲረዳ እራሱንም እየጠበቀ መሆን እንዳለበት መክረዋል። በግላቸውም እንደሚጠነቀቁ ገልጸዋል፡፡\n አዲስ ዘመን መጋቢት 17/2012 \n ለምለም መንግሥቱ", "passage_id": "8908f6bf9837626c5481bb5dc337072a" }, { "passage": "የሕክምና ባለሙያዎችን ልፋት እና ጥረት ምን ያክል እያገዝናቸው ይሆን?ብዙ ጊዜ ሰዎች በውስጣቸው የሚወዱት ሥራ ላይ ለመሰማራት ጥረት ያደርጋሉ፡፡ ተምረው ሲመረቁ ቀኝ እጃቸውን በማውጣት ለሕዝባቸው በተማሩበት የሥራ ዘርፍ ሕዝባቸውን በቅንነት በታማኝነት እና በአገልጋይነት መንፈስ ሊያገለግሉ ቃል ሲገቡ ይስተዋላል፡፡ ታዲያ ምን ያክልሉ በሥራቸው ሕዝባቸውን ሕይወታቸውን እስከመስጠት ለገቡት ቃል ታማኝ ሆነው እያገለገሉ ይሆን የሚለውን ለአንባብያን ትተን ከሰሞኑ ይህንን ተግባር ሲወጣ ሕይወቱን ስላጣው አንድ ግለሰብ ትንሽ እንበላችሁ፡፡ወቅቱ ዓለማችን በተላላፊው የኮሮና ቫይረስ በሽታ የምትናጥበት ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ታዲያ በፍርሃት እና በበሽታው የሚናጠው ሰው የትየለሌ ነው፡፡ ጉዳዩን አጢኖ ከባለሙያዎች የሚሰጠውን ምክር አንደ በአንድ በሕይወቱ የሚተገብረውም ቁጥሩ ቀላል አይደለም፡፡ባለታሪካችን ፈረንሳዊ ነው፤ ፈረንሳይ እና ጣልያን ወስጥ የኮሮና ቫይረስ ስለሚያስከትለው ጉዳት እና የጥንቃቄ መልእክት ሲተላለፍ አብዛኞቹ ይቀልዱ ነበር፡፡ መነሻውም ቻይና እንደመሆኑ እንዲህ በአጭር ጊዜ ሀገራቸው ገብቶ እንደሚያምሳቸው ያልገባቸው ሰዎች የሚሰጠውን ትምህርት ከቁብ አልቆጠሩትም ነበር፡፡ ታዲያ ብዙም ሳይቆይ የኮሮና ቫይረስ ፈረንሳይ እና ጣልያን ገብቶ ብዙዎቹን ለጉዳት ዳረገ፡፡ በዚህ ጊዜ ታዲያ ፈረንሳውያን የሕክምና ባለሙያዎች ሕዝባቸው ቀድሞ መልእክታቸው ባይሰማም በሽታው ከገባ በኋላ ግን በገቡት ቃል መሠረት ሕዝባቸውን ለማዳን ቀን ከሌሊት መልፋታቸውን ቀጥለዋል፡፡", "passage_id": "b5b0f30796f2bd65170dfa6742089ea0" }, { "passage": "በተደጋጋሚ በአገር ውስጥ የሚታዩ ችግሮችን ከመፍታት እንዲሁም በዘላቂነት ከማቆም አንጻር በመንሥት ዘንድ በሚወዱ እርምጃዎች የጎንዮሽ ጉዳቶች በሕዝብ እና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ተግዳሮቶች መፈጠራቸው የማይቀር ነው። በዚህም ረገድ በተደጋጋሚ ለሚፈጠሩ ችግሮች ኃላፊነትን ወስዶ ይቅርታ የሚጠይቅ ባለመኖሩ ችግሮች በተደጋጋሚ ሲከሰቱ ይስተዋላሉ።ጉዳዩ የተፈጠረው ከወደ ፀሐይ መውጫዋ አገር የትጉሀን መንደር በሆነችው የሩቅ ምሥራቋ አገር ጃፓን ነው። በጃፓን መዲና ቶኪዮ ታዲያ መነሻቸውን አድርገው ወደ ተለያዩ ጃፓን ከተሞች የሚወነጨፉ እጅግ ፈጣን እና ምቹ፣ ዘመናዊ ባቡሮች አሉ። በቅንጡ ባቡሮች ታዲያ ጃፓናዊያን በርካታ መቶ ኪሎሜትሮችን በየቀኑ እየተጓዙ ሠርተው መግባት የለመዱት እና የዕለት ተዕለት ተግባራቸውም ነው። እነዚህ ባቡሮች ታዲያ ጃፓናዊያን በራሳቸው ስብዕና የፈጠሯቸው እስኪመስል ድረስ ሽራፊ ሰከንዶችን ሳያዛንፉ ነው መንገደኞችን ለማጓጓዝ በእያንዳንዱ ጣቢያ ላይ ከተፍ የሚሉት።የሆነው ሆኖ ታዲያ በአንድ ወቅት ከጃፓናውያን ቅልጥፍና እና ሰዓት አክባሪነት አንጻር ሲታይ እጅግ እንግዳ የሆነ ነገር ተፈጠረ። ሰርክ በተቀመጠለት ደቂቃ እና ሰከንዶችን ሳያጓድል ከተፍ እያለ መንገደኞችን በጉያው አቅፎ የሚወነጨፈው ባቡር ለሦስት ደቂቃ ያህል ዘገየ። አንድ ደቂቃ ተጠበቀ፤ ለውጥ የለም፣ ኹለተኛው ደቂቃም አለፈ በቃ! ጃፓናዊያን ተጨነቁ። ሦስተኛው ደቂቃ ሞልቶ ሰከንዶች እንዳለፉ ታዲያ ተናፋቂው ባቡር ከተፍ አለ።ሰዓት አክባሪዎች፣ ሰከንዶች በሕይወታቸው ላይ ያላቸውን ጠቀሜታ ጠንቅቀው የሚያውቁት ጃፓናዊያን ከቅሬታ ወደ ቁጣ የቀረበ ስሜታቸውን መደበቅ ሳይችሉ ቀርተው በአደባባይ በመውጣትም ባቡሩን ለሦስት ደቂቃ የዘገየበትን ጉዳይ እንዲብራራላቸው መንግሥታቸውን ወተወቱ። ሥልጣኔ መቼም ደግ ነው! የጃፓን መንግሥት ሳይውል ሳያድር ነው የባቡሩን የሦስት ደቂቃ መዘግየት ምክንያትን መመርመር የያዘው።በቀኑ መጨረሻ ለካንስ አንድ ባቡር ብቻ ሳይሆን በአገሪቱ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ባቡሮች ነበሩ ዘግይተው ኖሮ፤ የተገልጋዮችም ቁጣ አይሎ ስለነበር ወደ ምክንያቱ የተሮጠው። አመሻሹ ላይ ታዲያ የጃፓን ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ወደ ሕዝብ በይፋ ቀርበው ለሦስት ደቂቃ የዘገየው ባቡር በኤሌክትሪክ መቋረጥ ምክንያት በመሆኑ ሕዝባቸውን ይቅርታ ጠየቁ። ይቅርታ መጠየቁ አስገራሚ ጉዳይ ቢሆንም የጠየቁበት መንገድ ደግሞ ግርምትን የሚያጭር ጉዳይ ነበር። ለሦስት ደቂቃ የዘገየውን ባቡር ታሳቢ በማድረግ ለሦስት ደቂቃ በሕዝባቸው ፊት ከወገባቸው እጅግ ጎንበስ ብለው ነበር ይቅርታቸውን ያቀረቡት።ይህን ጉዳይ በተለያዩ መንገዶች ከእኛ አኗኗር ጋር በማነጻጸር ከባድ እና ሩቅ ለሩቅ የሆንን እንደሆንን ለመታዘብ ታሪክ መጥቀስ እና መጽሐፍትን ማገላበጥ የሚገባ ጉዳይ አይደለም። ይህን ጉዳይ ያጫወተኝ ግለሰብ በሥራ አጋጣሚ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር እና ልዑካቸው በተገኙበት የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ምርቃት ላይ ከአዲስ አበባ ወደ አዳማ ባቡር ጉዞ ባደረግንበት ወቅት ነበር።ከጠዋቱ በኹለት ሰዓት አዲስ አበባ ለቡ የባር ጣቢያ የተነሳው ባቡር በኹለት ሰዓታት የመጎተት ሊባል በሚችል ፍጥነት ተጉዞ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ አንድ መቶ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው አዳማ ከተማ ላይ ተገኝቷል። ጉዞው ከባቡሩ መንቀራፈፍ እና በየደቂቃው እየጠነከረ ከሚሔደው ሙቀት ጋር ተዳምሮ ዝለትን ፈጥሮብን ነበር። ገና ከመጀመሪያውም በ1፡30 ጠዋት ላይ እንደሚጀምር የተነገረን ጉዞ ግማሽ ሰዓታትን እንደ ቀልድ አልፎ ነበር የተጀመረው።እናም ታድያ ለዚህም ይቅርታ የጠየቀ ካለመኖሩም በላይ በተለይም ደግሞ ከኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ኢትዮጵያ ተወካይ ከሆኑት ለሰማይ ለምድር የከበሩት ሥራ ኃላፊ በርሳቸው ምክንያት ማርፈዳችንን ከቁብ ሳይቆጥሩት ግማሽ ሰዓታትን አርፍደው መጥተው እንኳን በጊዜ ስለመጡ ውለታ እንደዋሉልን እና ምስጋና እና ሙገሳም እንዲቸራቸው በሚመስል አኳኋን ነበር ሲገረምሙን የነበረው። አጀብ ነው መቼም የእኛ ነገር።ይህን ጨዋታ ታዲያ ለማንሳት የተገደድኩበት ጉዳይ ከሰሞኑ የድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ ኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በእኛ እና እነርሱ ፖለቲካ አራማጆች ከፍተኛ ጉዳት ሲከሰት እና ውድመት ሲፈጠር መመልከት አሳዛኝ ነገር ነበር። በዚህ ብቻ ሳይበቃን ጭራሽ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሰላሟ በአንጻራዊነት ስትሞካሽ የነበረችው ሸገርም ሰኔ 23/2012 ስትናጥ ውላ ማደሯም አስገራሚ ጉዳይ ነበር።ታዲያ ይህን እና ያን ጉዳይ ተከትሎ በርካታ እርምጃዎች ከመንግሥት ወገን ሲወሰድ ታይቷል። እርምጃውም እንደቀጠለ ነው። ከተወሰዱት እርምጃዎች ታዲያ ኢንተርኔትን ጠርቅሞ የትኛውንም አይነት ግንኙነት ማገድ ነበር። በእርግጥ ለአገር ደኅንነት እና ለሕዝብ ሰላም ሲባል የተወሰዱትን እርምጃዎች በመንግሥት በኩል ይበል የሚያሰኙ ጉዳዮች መሆናቸውን ያህል፣ መንግሥት ጥርስ ማውጣት ጀምሯል አስብሎን ልባችንን በተስፋ ሞልቶናል።ግን ከኢንተርኔት መዘጋት ጋር በተያያዘ ለተፈጠረው ኪሳራስ ማነው ኃላፊነት የሚወስደው? ማነው እንደ ጃፓናዊው ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ወደ ሕዝብ ብቅ ብሎ ይህን ያህል ጊዜ ኢንተርኔት ያጠፋንባችሁ ለኹላችንም ጥቅም እና አገራዊ ደኅንነት ነው፤ በኢንተርኔት መጥፋት ሳቢያም ለተጋረጠባችሁ ችግር ኃላፊነቱን እኔ እወስዳለሁ የሚለን ሰው ማን ይሆን?\nኮቪድ 19 ከተከሰተ ወዲህ ሰው በቤት ውስጥ እንዲቀመጥ እና አስገዳጅ ካልሆነ በቀር ከቤት እንዳይወጣ የሚደረግበት አግባብ መኖሩን በተለያዩ መገናኛ ብዙኀን ስንታዘብ ቆይተናል። በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ይህን ትዕዛዝ የሚተገብሩ ግለሰቦች ወደ ውጭ በመውጣት የሚያስፈልጋቸውን ከመግዛት ይልቅ ኦንላይን ዕቃዎችን በማዘዝ ቤታቸው ድረስ እንዲመጣላቸው የማድረግ ጉዳይ እንዳለ ይታወቃል።አካላዊ ንክኪን ከማራቅ እና ማኅበራዊ ፈቀቅታን ከመተግበር አኳያ ታዲያ ትልቅ አስተዋጽኦ የነበረው ይኸው የኢንተርኔት ላይ ግብይት በአንድ አዳር ማስጠንቀቂያም ሳይሰጥበት ሲቋረጥ የኢሜይል ልውውጦች፣ የተጀመሩ ሥራዎች፣ ግብይቶች፣ ግንኙነቶች በአንድ ቅጽበት እንዲቆሙ ተገደዱ ማለት ነው። ይህ ደግሞ በወረርሽኙ ምክንያት ቤት ውስጥ ተቀምጦ የነበረውን ሰው በመሉ ወደ ገበያ ሥራዎች በመውጣት ራሱን ለበሽታ አጋልጦ ግብይት አንዲያካሒድ ማስገደዱም አንደኛው ተግዳሮት ነበር።እሺ! ታዲያ እንዲህ ላለው ችግርስ ይቅርታ የሚጠይቀው ማነው? በቃ የትኛውንም እርምጃ እየወሰዱ ጭጭ ዝም ማለት እንዴት ነው አገርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ የምናፋጥነው?የመልካም ሥራ ጅማሮዎችን በመጥቀስ እና በሌት ተቀን በማሞካሸት ወደ ተሻለ ደረጃ ከማሳደግ ይልቅ የተሠራውን ሥራ እያሞካሹ ምስጋና ይገባናል አይነት ከበሮ ሲደልቁ መዋል አገርን እንደ አገር ሕዝብንም እንደ ዜጋ ጠንካራ አድርጎ ለመገንባት እጅግ ከባድ የሆነ መንገድ እየተከተልን እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል። መሪ ሕዝብን እንደሚመስል ሁሉ ሕዝብም መሪውን እንደሚመስልም ማሰብ ያስፈልጋል።በተለይም ደግሞ ጥንካሬን ከመሪ ወደ ሕዝብ በማውረድ ጠንክሮ የሚያጠነክር፣ ተቋማትን ገንብቶ ማኅበረሰብን የሚያንጽ አመራር ያስፈልጋል። ጃፓናውያን ከብዙ መቶ ዓመታት የዝግመታዊ የማኅበረሰባዊ ልማቶች ዕድገትን አልፈው ነው አሁን የደረሱበት እና ያሉበት ደረጃ የደረሱት። የሠለጠነ ሕዝብ የሠለጠነ መሪን መፍጠር አያቅተውም።\nጃፓናዊያንም መብትና ግዴታቸውን በሚገባ ጠንቅቀው የሚያውቁ እና ለሚፈጠረው ችግር እና ለሚያጋጥመው ተግዳሮት ኃላፊነትን ወስዶ ይቅርታ የሚጠይቅ አካልን መፍጠር ችግሮች ተደጋግመው እንዳይፈጠሩ እና ትናንት የተቸገርንባቸው ነገ ደግሞው እንቅፋት እንዳይሆኑብን ማረጋገጫዎች ናቸው።ይህ ባልሆነበት እና ኃላፊነትን ወስዶ ተጠያቂነትን በማያሰፍን ማኅበረሰብ ውስጥ ስንኖር፣ የዘፈቀደ ምልልስ እና ሕገ ወጥ እና ሀይ ባይ ያጡ ድርጊቶች ማስተናገጃ ሜዳዎች ከመሆን አንላቀቅም። ኢንተርኔት መዘጋት አሁን የተፈጠረ ጉዳይ ሳይሆን ከዚህ ቀደምም ከአንድም ኹለት ሦስት ጊዜ ዘለግ ላሉ ጊዜያት ተጠርቅሞ ቆይቷል።በዚህ ወቅት ታዲያ በተፈጠረው ኢንተርኔት መቋረጥ እንደ መንግሥት ኃላፊነትን ወስዶ ኢንተርኔት በመቋረጡ ምክንያት የደረሱ ኪሳራዎችን አስመልክቶ ኃላፊነትን በመውሰድ ይቅርታ የጠየቀ ባለመኖሩ፣ ይኸው ዛሬም ተመሳሳይ ችግር እየተፈጠረ የማይለቅ አዙሪት ውስጥ ገብተን ስንዳክር እንገኛለን። ለመሆኑ መቼ ነው ይህ ጉዳይስ የሚቆመው? አሁንም ኃላፊነቱን ወስዶ ይቅርታ የሚጠይቅ የሠለጠነ የሥራ ኃላፊ ከሌለ በቀጣይ ይህ ችግር ላለመፈጠሩ ምንም አይነት ማረጋገጫ የለንም።በጃፓን ስለ ተፈጠረው አጋጣሚ በተመስጦ ሲያወጋኝ የነበረው የጉዞ አጋሬ ታዲያ የኹለተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በጃፓን ዮኮሐማ ከተማ እንደተከታተለ እና ወደ አገር ቤትም ተመልሶ በአንድ የጃፓን ዓለም አቀፍ ድርጅት ውስጥ ለዓመታት መሥራቱን አወጋኝ። እንዴት ነው ግን ከጃፓናዊያን ጋር መሥራት ስልም ጥያቄዎችን ሰነዘርኩለት። በጃፓናዊያን ዘንድ አንድ ደቂቃ የዓመት ያህል ዋጋ እንዳላት ሲነግረኝ በመገረም ነው ሳደምጠው የነበረው።በተቻላቸው መጠን ችግርን በመጋፈጥ እና መፍትሔ በመቅረጽ የሚያምኑ ሕዝቦች ሲሆኑ ኃላፊነትን በመውሰድ ለሚያጠፉት ነገርም ይቅርታን መጠየቅ እና በአጠፉት ጥፋትም በመጸጸት ከባድ ራስን መጉዳት ደረጃ ላይ በመድረስም የሚታወቁ ሕዝቦች እንደሆኑ አወጋኝ። እኔም ታድያ ምናለበት ባላቆመ እያልኩ ነበር የምሰማው። እንዲያው ጃፓናዊያንን እንደ ምሳሌ አነሳን እንጂ በሌሎች አገራትም ላይ ይህን መሰል ይበል የሚያሰኙ ተግባራት አይታጡም።እኛስ ከዚህ ምን እንማራለን? መቼ ነው የእኛ አመራሮች ወደ ሕዝብ ቀርበው ይህን እና ያንን ስለሠራን ይቅርታ እንጠይቃለን የሚሉን? መቼ ነው ሙሉ በሙሉ ኃላፊነቱን እኔ እወስዳለሁ የሚል የሥራ ኃላፊ የምናየው?ኹላችንም በእኔን አይመለከትም ልክፍት ተይዘን የሚፈጠረውን ጉዳይ እንኳን ምን እንደሆነ ሳናውቅ ጉዳዮ እኔን አይመለከትም በሚል ምላሽ ስንቱን ቀላል ችግር መፍትሔ አልባ ጋንግሪን አድርገነው ቁጭ አድርገነው ይሆን?በአጭር ለመቅጨት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ከኃላፊነት በመሸሻችን ምክንያት ለትውልድ ሲተላለፉ ማየት እንዴት የሚያሳቅቅ ጉዳይ እንደሆነ የተረዳነው አይመስለኝም። ካለንበት ድህነት ለመውጣት የሥራን ባህል ለልጅ ልጅ ከማውረስ ይልቅ ባልኖርንበት እና ባልነበርነት ዘመን ወደ ኋላ ሽምጥ ገስግሰን ዘር ስናጠና እና ሀረግ ስንመዝ ለድህነታችን የምናቀርበው ምክንያት ደግሞ ያለፈውን ዘመን አገዛዝ ሲሆን እጀግ ይገርማል። ዛሬም እኛ ትውልድ ላይ ይብቃ ብለን ለሚቀጥለው የልጅ ልጆቻችን እንዳይተላለፍ ለማድረግ እንኳን አልሞከርንም።ቅጽ 2 ቁጥር 89 ሐምሌ 11 2012", "passage_id": "c76a329c0c8113778204df10ca5e6336" }, { "passage": "እንደተለመደው በሥራ መውጫ ሰዓት ሰርቪስ ለመያዝ ተሰልፈናል። የአጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ ወደእኛ ሰፈር የሚሄደው መኪና ሁሌም በተሳፋሪዎች ይጨናነቃል። ብዙዎች የሾፌሩ ፍጥነትና የመንገድ ቆረጣ ስለሚመቻቸው ምርጫቸውን ለይተዋል። የባስ ካፒቴኑ ፈጣንና ቀልጣፋ ነው። መንገድ መርጦ መጓዝ ያውቅበታል።ከረጅሙ ሰልፍ መሀል ወንበር ለማግኘት የታደልነው ጎን ለጎን ተቀምጠን ጨዋታ ይዘናል። ተራው ያልደረሳቸው ደግሞ ከውጭ ወደውስጥ እያንጋጠጡ ነው። እንደእውነቱ ከሆነ ራቅ ያለ መንገድ ቆሞ መሄድ ከባድ ነው። እንደታክሲ ሦስት ሆኖ መቀመጥ ደግሞ አይሞከርም። እናም ከደጅ ያሉት ተንጠራርተው ቢያንጋጥጡ አይፈረድም።መቼም የመንገድ ላይ ወግ አይነቱ ብዙ ነው። አንዳንዴ ስለቤት ጣጣ ይወራል። አንዳንዴ ደግሞ ወቅታዊና አገራዊ ጉዳይ ሰፊ ሽፋን ያገኛል። ብዙ ጊዜ ግን አስራሁለት ሰዓት ላይ የሚደመጠውን ዜና መነሻ አድርጎ የሚከተለው አስተያየት ይበረክታል። ጥግ ይዘው የሚያንጎላጁት መንገደኞችም ከዕንቅልፋቸው በባነኑ ጊዜ የሚጨዋወቱት አያጡም።እሰይ! አሁን መንገዱን ገፋ አድርገነዋል። ፈጣኑ ካፒቴን እንደተለመደው በአጭር ጊዜ ረጅሙን ጎዳና አጋምሶታል። ሜክሲኮ አደባባይን ከመሻገራችን መጨናነቅ መጀመሩ ግን እንዳያስመሸን እየሰጋን ነው። ከኋላችን ደርሶ «እሪ» የሚለው አምቡላንስ ማለፊያ በማጣቱ ጨኸቱ ቀጥሏል። አንዳንድ መኪኖች ችግሩን ተረድተው ሊያሳልፉት እየሞከሩ ነው። ይህ መሆኑ ብቻ ግን እምብዛም መፍትሄ አልሆነም።\nየአምቡላንሱን ጨኸት ተከትሎ አዲስ ጨዋታ ተነሳ። አንደኛው የሚናገረው ከሌሎች በተለየ ነው። እርሱ አካባቢውን ስላወከው ድምጽ እምብዛም የተጨነቀ አይመስልም። መኪናው የታመመ ሰው ይዟል የሚለው እውነታም አልተዋጠለትም። እንደውም በስፍራው እንደተገኘ ሆኖ አሳማኝ የሚመስሉ ማሳያዎችን መምዘዝ ይዟል። የእርሱን ሀሳብ ተከትሎም ብዙዎች የራሳቸውን ግምት ማከል ጀምረዋል። በየወንበሩ ጨዋታው ደርቷል። አስተያየትና የግምት ሀሳብም እንዲሁ፤የእኔን ጆሮ የሳበው ግን ይህ አይነቱ ክርክር አልነበረም። ከጎኔ የተቀመጠችው ወይዘሮ በስልኳ በያዘችው ፎቶግራፍና ተያያዥ ታሪክ ልቤ ተማርኳል። ጉዳዩን በጥልቀት ስሰማው ደግሞ አእምሮዬ ርቆ ተጓዘ። በዚህ መሀል የብዘዎችን የተሳሳተ ግምት አሰብኩ። ራሴንም ገመገምኩ። እውነት ግን ስንቶቻችን በተሳሳተ እሳቤ እንመራለን? ስንቶቻችንስ ይህን በጎ ያልሆነ አመለካከት እንደያዝን እንገኛለን?ነገሩ እንዲህ ነው። አንድ ማለዳ ወደቤ ተክርስቲያን የሄዱት አባወራ ጸሎታቸውን አድርሰው ዞር ከማለታቸው ከአንድ ጎስቋላ አዛውንት ጋር ዓይን ለዓይን ይጋጫሉ። ሰውዬው ጥሩ ቁመና ቢኖራቸውም ኑሮ እንደጎዳቸው ያስታውቃል። ከላይ የደረቡት ልብስ አርጅቷል። ጫማቸው አልቋል። ችግር ያንገላታው መልካቸው ድካም ተጭኖታል።ከእርሳቸው አለፍ ብሎ ከተቀመጡት ባልንጀራቸው ጋር በልመና የሚያገኙትን ቁራሽ ይካፈላሉ። ለነፍስ ብሎ ሳንቲም የሚጥል ሲገኝም የተሰጣቸውን ተቀብለው ለሌላ ምጽዋዕት እጃቸውን ይዘረጋሉ። ልመና ለአዛውንቶቹ መተዳደሪያ ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።\nከሁለቱ ግን የአንደኛው ታሪክ ይለያል። ባገራቸው ቤት ንብረት አላጡም። ጥማድ በሬና የሚታረስ መሬትም አላቸው። እንደዋዛ አዲስ አበባን የለመደው እግራቸው ግን በቀላሉ አልመለሳቸውም። የልጆቻቸው ከተማ መዝለቅ ምክንያት ሆኗቸው ዋል አደር ማለት ለመዱ። ልጆችና እርሳቸው በአንድ ቤት አይኖሩም። ገሚሶቹ በቀን ሥራ ራሳቸውን ይደጉማሉ። የተቀሩትም በተመሳሳይ ሙያ ተሰማርተው ገንዘብ ያገኛሉ።አሁን አባትና ልጆች በአንድ ቤት ስለማይኖሩ አዋዋላቸውም ለየቅል ሆኗል። አባት በልመና ከሚያገኙት ገንዘብ የራሳቸውን ቤት ኪራይ ይከፍላሉ። ባገኟት ቁራሽ ሆዳቸውን ይችላሉ። በልመና ውሎ ህይወታቸውን ይመራሉ። ከማለዳ እስከምሽት በሚዘልቁበት አጸድ ብርድና ፀሐይ ብርቃቸው ሆኖ አያውቅም። ሁሉንም እንደአመጣጡ ተቀብለው የሰው ፊት ማየትን ከተለማመዱት ቆይተዋል።በቅርበት ሆነው ሁኔታቸውን ሲያስተውሉ የቆዩት አባወራ በአዛውንቱ ጉስቁልና ልባቸው በኀዘን ተነክቷል። ይህ ስሜት ብቻ ግን የበቃቸው አይመስልም። እርሳቸውን እያሰቡ ከቤት የተቀመጡትን ልብሶች ያስታውሳሉ። ካስታወሷቸው መሀልም ለእርሳቸው የሚበጀውን ይለያሉ። ይህን ሀሳባቸውንም ለአዛውንቱ ሲነግሯቸው ምስኪኑ ሰውየ ከልብ ተደሰቱ። እንዲህ አይነት ቅን አሳቢ ስላገኙም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ።አዛውንቱና አባወራው ወደቤት ከመሄዳቸው በፊት ጉዳዩን የሰሙት ባልንጀራቸው ጥያቄ አነሱ። እርሳቸውም እንደጓደኛቸው ቢለብሱ እንደሚወዱ ተናገሩ። አባወራው በጥያቄአቸው አልተከፉም። ሁለቱንም ሊያለብሷቸው ቃል ገብተው እንዲከተሏ ቸው አደረጉ።\nእኔና ወይዘሮዋ ጨዋታችንን ቀጥለናል። በግሌ የሰዎቹ ታሪክና የአባወራው ቅንነት እያስገረመኝ ነው። እግረመንገዴን በርካቶችን አሰብኳቸው። ቤት ንበረታቸውን ትተው፤ የሞቀ ትዳራቸውን ፈትተው ለልመና የተዳረጉ ቁጥር አልባ ወገኖች ትውስ አሉኝ ። ቤት ይቁጠራቸው እንጂ ብዙዎቹ ተመሳሳይ ህይወት ይጋራሉ። እያላቸው የሌላቸው ሳያጡ ያጡ ጎስቋሎች ጥቂት አይደሉም።ሦስቱ ሰዎች ጀሞ አንድ ከሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በአንደኛው ተገኝተዋል። አባወራው ከፊት ቀድመው ሁለቱ እየተከተሉ ነው። በቁምሳጥኑ ከተሰደሩት ሙሉ ልብሶች መሀል ያሰቧቸውን አውርደው ለአዛውንቶቹ መስጠት የጀመሩት ሰው ምስጋና እየደረሳቸው ነው። እነርሱም የተራበን ያበላ፣ የታረዘን ያለበሰ በሚለው ቃል መሰረት ቅን ላደረጉት አባወራ ምርቃት እያወረዱ ነው።አሁን ሁሉም ተጠናቅቆ ተሰነባብተዋል። ይህ ከመሆኑ በፊት ግን ዳግም ለመገናኘት ቀነ ቀጠሮ ወስደዋል። ከቀናት በኋላ አባወራው በቤታቸው የሚያደርጉትን ጠበል ጠዲቅ ምክንያት አድርገው እንዲመጡ ጠርተዋቸዋል። ሁለቱም ተጋባዞች ዕለቱን አልዘነጉም። እንዲህ አይነቱ ጥሪ ለእነሱ ከስንት አንድ ነው። አክብረው የሚጠሯቸውና እንደሌሎች በእኩል የሚጋብዟችውም ጥቂቶች ናቸው።ቀናት ተቆጥረዋል። በአባወራው መኖሪያ ለጠበል ጸዲቁ የሚሆነው ዝግጅት ተጀምሯል። የሚጠሩ ሰዎች ተለይተው የጎደለው ሁሉ ተሟልቷል። ሁሌም ዕለቱን አስበው የሚዘክሩት ባልና ሚስት በጥሪው የሚገኙ እንግዶች እንዳይረሱ ያስባሉ።አሁን ቀኑ ደርሷል። እንደተለመደው መላው ቤተሰብ በመስተንግዶው ተዋክቧል። እንግዶች ይገባሉ፣ ይወጣሉ። አባወራውና ወይዘሮዋ ቆመው ያስተናግዳሉ፤ ሰዎችን ይቀበላሉ፣ ይሸኛሉ። ከተጠሩት መሀል ቀኑን ያልዘነጉት አዛውንት በሰዓቱ ተገኝተዋል። እርሳቸው ከሌሎች ቀደም ብለው ቢገኙም እንደአመጣጣቸው ፈጥነው መውጣት አልፈለጉም። ወጪ ገቢውን እያስተዋሉ በዝምታ ተቀምጠዋል።ቀኑ ተጋምሶ ምሽቱ እንደተቃረበ የተጠሩት እንግዶች ቁጥርም ጋብ ማለት ጀመረ። ጥቂት ቆይቶም ቤቱ ጭር አለ። ይህኔ አዛውንቱ እንግዳ ከመቀመጫቸው ተነሱ። ተነስተውም መላው ቤተሰብ ወደ እርሳቸው እንዲመጣ ጠየቁ። ይህን የሰሙ ሁሉ ቃላቸውን አክብረው በአንድ ተሰባሰቡ። ቀኑ እየመሸ በመሆኑ አባወራውና ባለቤታቸው ማሰብ ጀምረዋል። የእርሳቸው ቤት ከአካባቢው የራቀ በመሆኑ እያስጨነቃቸው ነው ። እርሳቸው ግን ይህ ሁሉ ስሜት ምናቸውም አልነበረም።ንግግራቸውን በተለየ ምስጋና የጀመሩት እንግዳ እንባ እየተናነቃቸው እጃቸውን ወደጉያቸው ሰደዱ። ወዲያው ዳጎስ ያለ እስር በጣቶቻቸው መሀል ታየ። አዛውንቱ ያወጡትን ከማስረከባቸው በፊት ስለሆነው ሁሉ ተናገሩ። የዛን ዕለት አባራው ስለእርሳቸው አዝነው ሙሉውን ልብስ በሰጧቸው ጊዜ ቤታቸው ገብተው ልብሱን ሲለኩት በኮቱ የውስጠኛው ኪስ የታሰረ የብር ኖት ያገኛሉ።ብሩ ከለመዱት መጠን የበዛ በመሆኑ በድንጋጤ ክው ብለው ይቆያሉ። አዎን! አባወራው በተለገሳቸው ሙሉ ልብስ ውስጥ አስር ሺ ብር እንደታሰረ ተቀምጧል። ይህን ሲመለከቱ አዕምሯቸው ክፋት አላሰበም። ቅን አስቦ መልካም ላደረገ ማንነት ውለታው በበጎነት መመለስ እንደሚኖርበት ወስነው ብሩን እንደነበረ አስቀመጡት። ይህን እውነት ያጫወተችኝ ወይዘሮ ይህ ታሪክ በባለቤቷና በመኖሪያ ቤቷ ስለመፈጸሙ ሳውቅ ግርምታዬ ላቀ ።ሰውዬው ያስረከቡትን የአስር ሺ ብር ጥቅል ባለቤቷ ቆጥረው ሲረከቡም በፎቶግራፍ የቀረውን ምስል ተመልክቼ አረጋገጥኩ። ወዳጆቼ! እውነት እንነጋገር ከተባለ ምን ያህሎቻችን እንሆን ይህን መሰሉን ታሪክ የምንጋራው? ማንኛችንስ ነን ሰውን በልቡ ሳይሆን በልብሱ ብቻ የማንመዝነው? እኚህ ገንዘብና እንጀራ ናፋቂ አዛውንት ግን ይህን እውነት ፈጽመዋል። ሰዎችን በልብስ ብቻ ሳይሆን በንጹህ ልቦና ብቻ እንድንመዝንም አስተምረውናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2011መልካምስራ አፈወርቅ", "passage_id": "53d642158a8f272c4658dbff4dcacaaa" }, { "passage": "  ሁሉም ሰው በአንድ ወቅት ሕፃን ነበር፤\nያ የተፈጥሮ ሂደት ነው። በአካልም ሆነ በአዕምሮ ለጋ ሙሉ በሙሉም በሰዎች (በወላጅ ወይንም በአሳዳጊ) ጥበቃ ሥር ሆኖ ማደግን\nየማያውቅ የሰው ፍጡር የለም። “ክፉና ደግ መለየት የማይችሉ ህፃናት ገና በለጋ ዕድሜያቸው ካልተቃኑ\nበወደፊት ህይወታቸው ላይ ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ማስከተሉ የማይቀር ነገር ነው” ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች፤ የዕድሜ ደረጃ\nየአንድ ሰው ሁለንተናዊ ዕድገት መሠረት የሚጣልበት መሆኑን ሲያጠይቁ፤ ህፃናት በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የሚደርሱባቸውን ጥቃቶች ለመከላከልም\nሆነ ራሳቸውን ለመጠበቅ በአካልም ሆነ በአዕምሮ ዝግጁ እንዲሆኑ ከፍተኛ የሆነ የአስተዳደግ ክትትል እንደሚያስፈልጋቸውም ይናገራሉ።\nየማኔጅመንት ባለሙያና በቤተሰብ ህይወት አማካሪ የሆኑት አቶ ቃለክርስቶስ\nኃይሉ እንደሚሉት፤ የህጻናት ማንነት የሚቀረጸው ባደጉበት ማህበረሰብ ውስጥ ነው። ልጆች በሚያድጉበት ጊዜ በአንድ ቤት ውስጥ የተለያየ\nአስተሳሰብ ሲኖር ያንን አስተሳብ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ተጨማሪ አስተሳሰቦችን ሊያስተናግዱ ይችላሉ። የሀሳብ ልዩነቶች ለህጻናት በሚመጥን\nመልኩ መሆን አለባቸው። ህጻናት በቤተሰብ ውስጥ ሊያዩት የሚገባው አስተሳሰብ የጋራ የሆኑ እሴቶችን ሊያንጸባርቁ የሚችሉትን ነው።\nበውጭ ሊያከብሩት የሚገባውን ነገር በቤት ውስጥ ሊያገኙም ይገባል። በበጎ መልኩ የተቀነበበ የሀሳብ ብዝኃነቱን ቤት ውስጥ ማግኘት\nየሚችሉ ህጻናት ንጹህ ህሊናና ጽዱ አዕምሮ ኖሯቸው ማደግ ይችላሉ። ሲያድጉም የተለያዩ አስተሳሰቦችን ማስተናገድ የሚችሉ ይሆናሉ።\nሲያድጉ ሌሎችን እንዲያከብሩ የሚያደርግ ድልድይ መስራት ያስፈልጋል። በመሆኑም፤ በቤት ውስጥ የሚንጻበረቁ አስተሳሰቦች የአንዱን\nኮናኝ የአንዱን የበላይ የሚያደርግ ሳይሆን በመከባበርና መደማመጥ ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት። ጤናማ ሀሳብ ከግለሰብ ጀምሮ እስከ ማህበረሰብ አካባቢያችን የተቀበለው\nመሆኑን የሚናሩት አቶ ቃለክርስቶስ፤ የጤናማ አስተሳሰብ ፍልስፍና በህብረተሰቡ ውስጥ በእምነትም በመንፈሳዊ አስተምሮም ተቀባይነት\nያገኘ መሆኑንና በህግ ከተደነገገው የሥነ ምግባር መር ጋር የማይጻረሩ ናቸው በማለት፤ መነሻቸውም ማህበረሰቡ መሆኑን ጠቅሰው፤ እነዚህን\nእውቅና ያገኙ በጎ ምግባራትና እሴቶች በህጻናት አዕምሮ ውስጥ እንዲሰርጹ ማድረግ ቀዳሚው ተግባር እንደሆነ ይገልጻሉ። ታዳጊዎች\nይህንን እንዲገነቡ ደግሞ ቤተሰብ አስቀድሞ ነገሩን መገንዘብ እንዳለበት ይመክራሉ። ወይዘሮ ገነት የማነ በትምህርት ተቋማት ዙሪያ የትምህርት ባለሙያ ናቸው። “ቤተሰብ ልጁን በስነ ምግባር፤ በተለያዩ\nስልቶች እንደሚገነባው ሁሉ ቅብብሎሹ ግን እስከ ትምህር ቤተ ደረጃ ድረስ መሆን ይኖርበታል፤ ሲሉ የትምህርት ተቋማትና የቤተሰብ\nትስስር መጉላት እንዳለበት ያስገነዝባሉ። በተለይም ለህጻናት ምቹ ሆኖ ማደግ ትምህርት ቤቶች ለህጻናት ከሚያስፈልገው ሥነ ልቦናዊ\nየአስተዳደግ ዘዴ ባሻገር በቁሳዊ ነገሮች ላይም ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ይናገራሉ። ልጆች የ“እችላለሁ” መንፈስ በውስጣቸው እንዲዳብር በሚገባቸው ነገር ማስተማር እንደሚያስፈልግ የሚመክሩት ወይዘሮ\nገነት፤ “ትምህርት ቤት ግልጽ ሆነው በተዘጋጁ የትምህርት መርጃ መሣሪያዎች መደራጀት እንዳለበትና፤ በክፍል ውስጥ የሚገኙ ዕቃዎች\nቦታቸውን በአግባቡ ካገኙ ክፍሉ ምንጊዜም ለሕፃናት መልክና ሥርዓት ያለው ሆኖ እንዲታያቸው ይሆናል” ይላሉ። ይህና መሰል ምቹነት\nያላቸው ሁኔታዎች ልጆች በሁሉ ነገር ምጡቅ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል። ወይዘሮ ገነት፤ “የግብረ ገብነቱ እሳቤ ደግሞ ከቤተሰብ አልፎ በትምህርት ቤት ውስጥ ሊዳብር ይገባል። የትምህርት\nተቋማት በተለይ መልካም እሴቶችን ማስተማር ብቻ ሳይሆን እንደ ባለቤትነት መያዝ ይኖርባቸዋል። ቤተሰብ የሚመክረውን ካልኖረው ልጆች\nሊኖሩት እንደማይችሉት ሁሉ፤ ትምህርት ቤቶችም የሚያስተምሩትን በተግባር ማሳየት ይኖርባቸዋል። የእያንዳንዱ ትምህርት ተቋም ማህበረሰብ\nለተማሪዎች የሚመጥን መልካም አርዓያነታቸውን መግለጥ አለባቸው። የሥነ ሥርዓት ደንቦችን ከቀረፅን በኋላ ለተግባራዊነታቸው በአቋማችን\nመፅናት ይጠበቅብናል። አለበለዚያ ማስተማሩ ብቻውን ለውጥ አያመጣም” በማለት ያብራራሉ። እንደ እርሳቸው ማብራሪያ፤ የሕፃናት ባህሪይ ትክክለኛ መስመር እንዲይዝ የመምራትና አቅጣጫ የማሳየት ጉዳይ\nነው። በመሆኑም ልጆች ትምህርት ቤት የሚሄዱት ሊማሩ እንጂ ሊፈረድባቸው አይደለም። ሌላ ሰው ለመሆን ከመማቀቅ መውጣት አለባቸው።\nፈተናዎች አለማወቅን የሚያሳዩ መሆን የለባቸውም። ህጻናት ራሳቸውን እንዲያገኙ መፍቀድም ይገባል። በግለሰብ ደረጃ የሥነ ልቦና ባለሙያ የሆኑት ወይዘሮ ሰብለ ሀይሉ በበኩላቸው፤ የሰው ልጅ በህይወቱ ስኬታማ\nይሆን ዘንድ ወሳኝ የሆኑት አዕምሮን የማጽዳት ተግባራት ሲሆኑ፤ ይህም ከህጻንነት ዕድሜ ጀምሮ ሊሠራ የሚገባው ነው። በተሰማሩበት\nየህይወት ደረጃ አስተሳብን ማጽዳትና ስሜትን መረዳት ቤተሰባዊ ከሆነው የኑሮ ደረጃ ይጀምራል። ሰው ከቤተሰብ ጀምሮ የራሱን ማንነት\nሊያዳብር ይገባዋል። በቤተሰብ የሚዘራውን መልካምነት የሚያዳብረው ደግሞ ትምህርት ቤትና አካባቢ ነው ይላሉ። ወይዘሮ ሰብለ እንደሚሉት፤ የራስን ማንነት ከሚጎዱ ነገሮች መካከል አንዱ መልካም ያልሆነ ቤተሰባዊ ግንኙነት\nነው። ስድብ፣ ክርክር. ጭቅጭቅና መሰል አሉታዊ ጉዳዮች በቤት ውስጥ ሲስተዋሉ ልጆች ይህንን እኩይ ባህሪይ ይዘው ከማደጋቸው ባሻገር\nየበታችነት ስሜት እንዲሰማቸውም ያደርጋል። በመሆኑም በፍርሀት፤ በጥርጥሬና በስጋት ሊያድጉ ስለሚችሉ ከሁሉ በላይ ፍቅር መስጠት\nያስፈልጋል። “ዓይናችንን ብንገልጥ በምንኖርበት አካባቢ በቀላሉ እንደ\nባህልና ልምድ የተቀበልናቸው በርካታ የሰውን ልጅ ህልውና የሚያቃውሱ ብዙ ድርጊቶችን እናገኛለን። ጉዳዩን በእኔነት መንፈስ በመመልከት\nሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት” ብለዋል ወይዘሮ ሰብለ፤አዲስ ዘመን መስከረም 2 ቀን\n2012 ዓ.ም አዲሱ ገረመው", "passage_id": "2704626c714d51be6f4f2c01d3fbfefa" } ]
84890908414bfdd95d7d6fc9b1e96f47
29bb3ebfc54c214f56a34622c0f6eab9
“ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አልጠፋም’’ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አልጠፋም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ትናንት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከመተከል ዞን ነዋሪዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት፤ ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አለመጥፋቱን የገለጹ ሲሆን፤ ምንም እንኳን ጠላቶች በዚህ መልኩ ቢሰሩም አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮች እንዳይደገሙ አድርገን እንፈታዋለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡“ከመተከል ነዋሪዎች ጋር ባደረግኩት ውይይት ሕዝባችን ለአንድነት፣ ለሰላም፣ ለልማት እና ለብልጽግና ያለው ፍላጎት የትኛውንም የመከፋፈል አጀንዳ እንደሚያከሽፍ ተመልክቻለሁ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ በመሆኑ ምክንያትም ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን በጎሳ እና በሃይማኖት የመከፋፈል ፍላጎታቸው አሁንም ድረስ ቢኖርም ይህ ፍላጎታቸው እንዳልተሳካላቸው ገልጸዋል። ይሄንን ጽኑና አስተዋይ ሕዝብ ይዞ ደግሞ ችግሮችን እንዳይደገሙ አድርጎ መፍታት እንደሚቻልም ተናግረዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፣ የሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፤ በመድረኩ ላይ በአካባቢው የተከሰተውን የፀጥታ ችግር መፍታት በሚቻልበት አግባብ ላይ ውይይት የተካሄደበት መሆኑንም ነው ኢዜአ የዘገበው። በተያያዘ፣ ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት እንደዘገበው፤ ውይይቱ መድረኩ በመተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮችን ለማስቆም ዘለቄታዊ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ሲሆን፤ በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለሀገሪቱ አንድነትና ሠላም ብቸኛው አማራጭ ኢትዮጵያውያን ከጥላቻ፣ ከስሜት እና ከመገፋፋት ወጥተው አንድነታቸውን እና አብሮነትን ማጠናከር ነው ብለዋል። በቀጣናው የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር በዘላቂነት ለማስቆም ጥረት የተደረገ ቢሆንም በርካታ ተዋናዮች በመኖራቸው ችግሩን በአፋጣኝ እንዳይቆም አድርጎት መቆየቱንም ገልጸዋል። በመሆኑም አካባቢውን ወደ ሠላም የመመለሱ ሥራ በትኩረት እንደሚሠራ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ባለፈ ግን በዞኑ እየተካሄደ ያለው የህግ ማስከበር ተግባር ገለልተኛ እና ከአድሏዊነት በፀዳ መልኩ እንዲተገበር አሳስበዋል። በስሜት እና በብሶት የጁንታውን የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ ወደ ጫካ የሸሸው ኃይል በሠላማዊ መንገድ እንዲመለሱ ለማድረግ አመራሩና በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።ከዚህ ባለፈ የክልሉን የተፈጥሮ ፀጋ በመጠቀምሥራ አጥ ወጣቶችን በማደራጀት የክልሉ መንግሥት ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እንዲሰራም መልዕክት አስተላልፈዋል። መንግሥት እየወሰደው ካለው እርምጃ ባሻገር በቀጣናው ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶች ጋር በዞኑ የተፈጠረውን የሠላም እጦት ለመፍታት ያላሰለሰ ጥረት እንዲያደርጉም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ ያቀረቡት።የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ኃላፊነት የጎደለው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም እና ባለፋት 27 አመታት የህወሓት ጁንታ የፈፀመው የፖለቲካ አሻጥር በቀጣናው ዘላቂ ሠላም እንዳይረጋገጥ አድርጎ መቆየቱን ተናግረዋል። በመተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚፈጠረውን የጸጥታ ችግር ለማስቆም ጥረት ቢደረግም፤ አባባሽምክንያቶችን ለይቶ መፍትሄ መስጠት ባለመቻሉ የፀጥታ ችግሩ እስካሁን መቀጠሉን አንስተዋል።ዞኑ የተለያዩ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ለዘመናት በአብሮነት የሚኖሩበት አካባቢ እንደመሆኑ መጠን፤ የህዝቦችን አንድነትና አብሮነትን ለማጠናከር መንግሥት በትኩረት ሊሠራ ይገባልም ሲሉ ነው ተሳታፊዎቹ ያስገነዘቡት።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37919
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦነግ ሸኔ እና በወያኔ የጥፋትና የሽብር ሴራ ኢትዮጵያ እንደማትፈርስ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለፁ።አቶ ሽመልስ አብዲሳ የሰጡት መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።የሀገራችን ህዝቦች ለዴሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለፍትሃዊ ተጠቃሚነት በጋራ እየታገሉ መስዋእትነት እየከፈሉ በጋራ ተጉዘዋል፤ አሁም በመጓዝ ላይ ይገኛሉ።የህዝቦች የጋራና ትግልና መስዋእትነት ፍሬ አፍርቶ ሃገራችን የለውጥ ሂደት ውስጥ ገብታለች። ሆኖም በዚህ የለውጥ ሂደት በህዝቦች ትግል ድል የተነሱት ጨቋኝ ክንዳቸው እንዲሰበሰብ፣ የብዝበዛ መረባቸው እንዲበጣጠስ የተደረገው ሴረኛው የወያኔ ቡድን ባለፉት 27 ዓመታት ላደረሳቸው ጥፋቶች መፀፀትና መታረም ሲገባው አሁንም የተካነበትን ሴይጣናዊ የተንኮል ተግባሩን አጠናክሮ ቀጥሎበታል።ይህ ቡድን እንደለመደው ህዝብን ከህብ በማጋጨት ደም በማፋሰስ፣ በሚፈጠረው የፖለቲካ አለመረጋጋት ከቻለ ከተገፋበት የማዕከል ስልጣን መመለስ ካልቻለ የሚመቸውን አሻንጉሊት መንግስት ለማቋቋም በተለመደው አይነ ደረቅነቱን የቀን ቅዠት ውስጥ በመግባት ሌት ተቀን ሴራ በመጎንጎን ላይ ይገኛል።ከወያኔ እኩይ የሴራ ድርጊቶች መካከል ዋነኛው ለፖለቲካ ትርፍ ሲባል ህዝብ ከህዝብ በማጋጨት በንጹሃን ደም መነገድ ነው።በተለይም ደግሞ የኦሮሞና የአማራ ወንድማማች ህዝቦች መካከል ግጭት ለመፍጠር መሞከር የሰርክ ተግባሩ ነው።ይህ ሙከራዉ አልሳካለት ሲለዉ የኦነግ ሸኔ አሸባሪ ቡድንን በማስታጠቅ የሎጀስቲክና የፋይናን ድጋፍ በማድረግ በትሮይ ፈረስነት በመጠቀም በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት በማስፈጸም የሃገራችንን የለውጥ ተስፋ ለማጨለም እየተፍጨረጨረ ይገኛል።አሸባሪው የኦነግ ሸኔ ቡድን ባለፉት ሁለት አመታት በህዝብና በመንግስት የፀጥታ ሃይሎች ትብብር እየተወሰደ ባለው እርምጃ በከፍተኛ ሁኔታ አከርካሪው ተመትቶ በመንኮታኮት ላይ ይገኛል።ይህ በህዝብና በጸጥታ አካላት ክፉኛ እየተመታ ያለው ቡድን ተስፋ ወደ መቁረጥ በመግባቱ, እንዲሁም ከወያኔ የሚሰጠውን ተልዕኮ በመውሰድ ሰላማዊ ዜጎችን አርሶ አደሮችን በየደረጃው ያሉ የመንግስት አመራሮች ላይ የሽብር ጥቃት ወደ መሰንዘር ተሸጋግሯል።በትላንትናው እለት ማታ በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ጋንቃ በተባለው ቀበሌ ዜጎቻችን ላይ የሽብር ጥቃት በማድረስ በሰው ህይወት እና አካል ላይ ጉዳት አድርሰዋል።በዚህ የሽብር ጥቃት ዉድ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘን እየገለፅኩ የተፈጠመውን፤የሽብር ጥቃት አጥብቄ አወግዛለሁ።በዚህ አጋጣሚ በኦነግ ሸኔ አሸባሪ ቡድን ላይ እየተወሰደ ያለው ውጤታማ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ላረጋግጥ እወዳለሁ።እንደዚህ አይነት የፈተና ወቅት የህዝቦችን ወንድማማችነትና በጽናት አብሮ በመቆም ፈተናን የማለፍ ልምድን ያጠናክራል እንጂ ጠላት እንደተመኘው ህዝቦችን የሚያባላ ፈጽሞ አይሆንም፡፡እንደ መንግስትም አስፈላጊዉን መስዋዕትነት በመክፈል የህዝቦችን ወንድማማችነት እና የኢትዮጵያን አንድነት የማስቀጠል ተግባር አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡በኦነግ ሸኔ እና በወያኔ ሽብር እና የጥፋት ሴራ ኢትዮጵያ አትፈረስም።ሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ርእስ መስተዳድር", "passage_id": "deaab60bea55800fb14d55c1921c0a2d" }, { "passage": " አዲስ አበባ፡- የኢህአዴግ እህት ድርጅቶች የሆኑት አዴፓና ህወሓት ያሉባቸውን አለመግባባቶች ተቀራርበው በመፍታት የታገሉለትን አላማ እውን ሊያደርጉ እንደሚገባ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ አሳሰቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከትናንት በስቲያ\nበሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ ሁለቱ ፓርቲዎች የታገሉበት ዋና አላማ ለህዝባቸው ልማት፣ ሰላምና፣ ዴሞክራሲን ለማምጣት\nቢሆንም ይህ አላማ በተሟላ መንገድ በሁለቱ ህዝቦች ላይ አልተሳካም። በመሆኑም አላማቸው እስካልተሳካ፣ በጉዞ ሂደት ላይ አስካለ\nድረስ በመካከላቸው ያለውን አለመግባባት በመፍታት ተጨማሪ የጋራ ጥረት ማድረግ ይኖርባቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢህአዴግ አባል\nድርጅቶች መካከል ስላለው አለመግባባት ተጠይቀው «ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አዴፓና ህወሓት በመግለጫ መነጋገር ከጀመሩ በኋላ ወዴት እያመራን\nነው የሚል ሥጋት እንደተነሳ እኔም አውቃለሁ» በማለት ገልፀዋል። አያይዘውም አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ማንኛውንም\nእርምጃ ሲወስድ እንደ መስፈርት መያዝ ያለበት ሁለት መሰረታዊ ነገሮች መኖራቸውን አመልክተው፤ የመጀመሪያው ፖለቲካል ሞራሊቲና ፖለቲካል\nእሴት መሆኑን ጠቁመዋል። ይህን እርምጃም በመውሰዱ ከፖለቲካል እሴት አንፃር ምን ልማትና ምን ጥፋት ሊያመጣ ይችላል ብሎ ማሰብ\nየሚጠበቅበት መሆኑን አስረድተዋል። በሁለተኛ ደረጃም ሊመጣ የሚችለውን ውጤት ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።\nበዚህ ረገድም የህወሓት መግለጫ፣ ድርጊትና ማንኛውም እንቅስቃሴ ለትግራይ ህዝብ ከዚያም አልፎ ለኢትዮጵያ ህዝብ\nከሚያስገኘው ጥቅም አንፃር የሚመዘን መሆኑን አብራርተዋል። «አዴፓም የሚያወጣቸው ማንኛውም መግለጫዎች ለአማራ ህዝብ ከዚያም አልፎ\nለመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ከሚያስገኘው ጠቀሜታ አንፃር ይመዘናል። ከዚህ አንፃር የመግለጫ ምልልሱን እራሱን አስችሎ ማየት ይኖርብናል።\nእንደ ባህሪይ ግን ብዙ አዲስ ባህሪይ አይደለም» በማለት ተናግረዋል።ከዚህ ቀደም አዴፓ እና ህወሓት በመግለጫና በይፋ አይነጋገሩ\nእንጂ ከዚህ በባሰ በዝርዝርና ጠንከር ባለ መንገድ በመድረኮቻቸው ይነጋገሩ እንደነበር ያመለከቱት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ አሁን አጠቃላይ\nየፖለቲካ አውዱ በመቀየሩ ማንኛውም ነገር መነገር ከመጀመሩ ጋር ተያይዞ መምጣቱን አስገንዝብዋል። «አንድ የፖለቲካ ፓርቲ የራሱ\nአላማ የራሱ ሀሳብ አለው። ያን ፍላጎቱና ያ ሀሳቡን ለማሳካት አጋር ሊሆን የሚችል ሀሳቡን ተጋርቶ ወደፊት ድጋፍ ሊሰጠው የሚችል\nአጋር ይፈልጋል» ብለዋል። በዚህም ህወሓትና አዴፓ ከዚያም ደኢህዴን በኢትዮጵያ ውስጥ ፓርቲዎች ሁሉ በላይ በትብብር በወንድማማችነት\nስሜት አብረው መታገላቸውን አስታውሰዋል። «እንኳን ፖለቲካ ውስጥ በሌላ መስክም ስንሳተፍ እንደዚ አይነት ንትርኮች ያጋጥማሉ። አንዳንዴ የፖለቲካ\nፓርቲዎች ንግግሮቻቸውን ደብቀው ይነጋገራሉ። ለህዝብ ቢገለጥ እምብዛም ጥቅም የሌለው ከሆነ አንዳንዴ ደግሞ በአቋማቸው ህዝባቸውን\nለማሰለፍና ለማስከተል ግልፅ ያደርጋሉ። የፓርቲዎቹ መግለጫ በዚያ መንገድ ባይሆን ይመረጥ ነበር» በማለት ተናግረዋል። እነዚህ ንትርኮች\nበሰለጠነ መንገድ በድርድርና በውይይት መፍታት እንደሚያስፈልግ አስገንዝብዋል። እንደ ጠቅላይ\nሚኒስትሩ ማብራሪያ፤ በህወሓትና በአዴፓ መካከል የተፈጠረውን ምልልስ እንዴት እንፍታው ብለው መፍትሄ አምጪ ንግግር ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።\nበዚህም ሌሎች የኢህአዴግ እህት ድርጅቶች ለሁለቱ ፓርቲዎች መድረክ ፈጥሮ ሀሳቦቻቸውን እንዲያንሸራሽሩና እያንዳንዱ ቡድን ላይ የታየውን\nጥፋት እራሱ ሂስ ማድረግ እንዲችል ዕድል መፍጠር ይገባቸዋል። ይህንን ማድረግ ከተቻለም ይበልጥ መቀራረቡ ይመጣል፤ መፍትሄ ማስቀመጥ\nከተቻለም በህዝቦች መካከልም ሆነ በፓርቲዎች መካከል ያሉ ልዩነቶች ይፈታሉ። ይህንን ማድርግ ካልተቻለ ግን ጉዳዩ እየተካረረ ይመጣል።ማህሌት አብዱል", "passage_id": "58e1986137742505d0732adf981c4f40" }, { "passage": "በኦሮሚያና በኢትዮጵያ ሶማሌ የተፈጠረው ግጭት \"ያልተገባ፣ ከኢትዮጵያዊነት ባህል ያፈነገጠና የሁላችንንም አንገት ያስደፋ የሽንፈት ታሪካችን ነው\" ሲሉ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አሕመድ ገለጹ ። በጅግጅጋ በክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና በከተማዋ ህዝብ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከክልሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከተውጣጡ ነዋሪዎች ጋር ከትናንት በስትያ ውይይት አድርገዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ባደረጉት ንግግር ከወራት በፊት በኢትዮጵያ ሶማሌ ና በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ የተፈጠረው የእርስ በርስ ግጭት የሰው ህይዎትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ጠቅሰው፤ በግጭቱ ሁለቱም ወገን ተሸናፊ እንደነበሩ ገልጸዋል ፡፡\"ያለፈውን ችግር የምንቋቋምበት የዳበረ የአብሮነት ባህል አለንም \"ነው ያሉት ።ጠባሳው ፈጥኖ እንዲሽር ችግሩ የማያዳግም እልባት እስከሚያገኝበት ዳርቻ ድረስ ባለን አቅም ሁሉ በርትተን በጋራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተከስቶ የነበረውንና ከኢትዮጵያዊነት ልማድ ያፈነገጠ ክስተትም ዘመናትን በተሻገረው የአብሮነት ትውፊት እንደሚወጡትም እምነታቸውን ገልጸዋል ።የተፈጠረው ችግር ከዚህ በኋላ ውሎ ሳያድር በማያዳግም እርቀ ሠላም እንዲቋጭም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ሶማሌና በኦሮሚያ ክልል ሕዝቦች መካከል ያለው ወሰን አስተዳደራዊ መለያ ከመሆን ባለፈ የልዩነት መነሻና የግጭት ምክንያት ሊሆን እንደማይገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።ሁለቱ ህዝቦች ደስታንና መከራን ከትውልድ ትውልድ እየተቀባበሉ ያሳለፉትን የረጅም ዘመናት አብሮነትም ሕዝባዊ ገጽታ እንደተላበሱ ወደፊት እንደሚቀጥሉም አስረድተዋል።መንግስት በአጭር ጊዜ ውስጥ ችግሩን እንደሚፈታ በማረጋገጥ፥ ከሁለቱም ክልሎች የተፈናቀሉ ዜጎችን በፍጥነት ወደ ነበሩበት መልሶ የማቋቋም ስራ እንደሚከናወንም አስታውቀዋል።የሁለቱ ክልል ህዝቦች አብሮነትና ወንድማማችነትም ትናንት የነበረ፣ ወደፊትም የሚዘልቅና ይበልጥ የሚያብብ መሆኑንም ጠቅሰዋል።በመሆኑም በሁለቱ ክልሎች መካከል የነበረው የአንድነት መንፈስ ወደ ቀድሞው እንዲመለስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣና የመፍትሄው አካል እንዲሆንም ጥሪያቸውን አቅርበዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ዛሬ የምትራመድበት የሠላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉዞ መላው ኢትዮጵያውያን በከፈሉት መስዋዕትነት የተገኘ መሆኑን ጠቅሰዋል።በሠላምና በመረጋጋት ድባብ ውስጥ መተባበር ከተቻለም ድህነትን ማሸነፍ እንደሚቻልም አስገንዝበዋል ።ባለፉት ዓመታት የሠላም፣ የዴሞክራሲና ልማት ስኬቶች መመዝገባቸውን ነው ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡(ኤፍ ቢ ሲ)", "passage_id": "b40245e2377175c9f29c41f6eae9497a" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አንድ ወደፊት ስንሄድ ሁለት ወደኋላ የሚመልሱንን ሀይሎች ማስቆም እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ አሳሰቡ።የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዛሬው እለት ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በመግለጫቸውም ከሰሞኑ በተከሰተው ግጭት የ86 ሰዎች ህይወት አልፏል ያሉ ሲሆን፥ ከሟቾች መካከል 82 ወንድ፣ 4 ሴቶች መሆናቸውምን አስታውቅዋል።በብሄር ደግሞ 50 ኦሮሞ፣ 20 አማራ፣ 8 ጋሞ፣ 2 ስልጤ፣ 1 ጉራጌ፣ 2 ሀዲያ እና አንድ አርጎባ ሲሆኑ፥ የአንዱ ሟች ብሄር እንዳልታወቀም አስታውቀዋል።በሀይማኖት ደግሞ ከሟቾቹ መካከልም 40 ክርስቲያን ሲሆኑ፥ 34 ሙስሊም እና 12 የሌላ እምነት ተከታዮች መሆናቸውንም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በመግለጫቸው ያስታወቁት።ከሟቾቹ መካከል 76 ሰዎች በእርስ በእርስ ግጭት፤ 10 ሰዎች ደግሞ በፀጥታ ሀይሎች ህይወታቸው ማለፉንም ገልፀዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በመግለጫው፥ ይህ ክፉ ክስተት በኢትዮጵያ የግጭት እሳት ሲነሳ አንዱን ክፍል አቃጥሎ ሌላውን አሙቆ የሚያልፍ እንዳልሆነ ያሳየ ነው ብለዋል።መንግስት የፖለቲካ እና የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ ሆደ ሰፊነቱን አብዝቶ ሲያስታምም ከርሟል ብለዋል።ከሀይልና ጉልበት ይልቅም፤ ትምህርት እና ምክክር ይሻላል ብሎ መታገሱን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፥ ትእግሰቱ ፍርሃት፤ ማስታመሙ ድካም፣ የመሰላቸው ካሉ ግን ተሳስተዋል ብለዋል።አንዳንዶች እንዲማሩ ተብሎ ሰፊ ልብ እና ትክሻ ሲሰጣቸው አጋጣሚውን ሳይጠቀሙበት ቀርተው የዜጎች ህይወት ለአደጋ የሚጋለጥበት ምክንያት መፈጠሩንም አንስተዋል።መንግስት የዜጎችን እና የተቋማትን ደህንነት ለመጠበቅ የሀገሪቱ ህግ ባስቀመጠው መሰረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል።በአንድ በኩል የፖለቲካውን እና የዴሞክራሲውን ምህዳር ለማስፋት፤ በሌላ በኩል ደግሞ ፍትህንና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እንደሚሰራም አስታውቅዋል።“ያለፉትን ስህተቶች ለማረም እየሰራን በሌላ በኩል ደግሞ ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ ህጋዊና ተመጣጣኝ እርምጃ እንወስዳለን” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፥ በዚህ አግባብም አልሚ ሁሉ ስራውን፤ አጥፊ ሁሉ ደግሞ በጥፋቱ ልክ ተጠያቂ እየሆነ እንደሚሄድም አስታውቅዋል።የሀይማኖት አባቶች፣ የጎሳ መሪዎች፣ የፖለቲካ ልሂቃን፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ እናቶች፣ ወጣቶች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች መንግስት የሀገሪቱን ሰላም፣ ደህንነት እና አንድነት ለማስጠበቅ ሲል ህግና ስርዓትን እንዲያስከብር ደጋግመው መጠየቃቸውን በማንሳት፥ ጥያቄያቸው ተገቢ መሆኑን እና መንግስትም ህግ የሚፈቅድለትን ሁሉ ለማድረግ አቅምም፣ ዝግጁነትም፣ ብቃትም እንዳለው አስታውቅዋል።የፀጥታ አካላትም የሀገርን ሰላም፣ ደህንነት፣ የህዝቦችን አብሮ መኖርና አንድነት፣ የተቋማትንና የኢንዱስትሪዎችን ደህንነት በህግ አግባብ የመጠበቅ ግዴታቸውን እንዲወጡም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አሳስበዋል።የፍትህ አካላትም ለአጥፊዎች ትምህርት፤ ለተጎጂዎች ካሳ የሚሆን የተፋጠነ ፍትህ በማስፈን ፍትህን እንዲያረጋግጡ ጥሪ አቅርበዋል።ዋልታ ረገጥ የብሄር እና የእምነት ጫፍ ላይ ቆመው ችግሮችን የሚያባብሱ ወገኖችም አስተያየቶቻቸው እና መልእክቶቻቸው ተጨማሪ እልቂትና ጥፋት ከሚያመጣ ማናቸውም ተግባር እንዲቆጠቡም አሳስበዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፥ “ነገሩን ሁሉ በስሜትና በወገንተኝነት መለኪያ ብቻ ሳንመለከት፤ ከስሜት በላይ ሆነን የተጋረጠብንን አደጋ በብልሃት መቀልበስ እንድንችል የዘወትር ትብብራችሁ እልዳይለየን እጠይቃለሁ” ብለዋል።በአላዛር ታደለ", "passage_id": "4e23192770001fee09b84c8c1f980878" }, { "passage": "አዲስ አበባን የሚኖሩባት ሳይሆን ሁሉን መሰብሰብ የምትችል አድርገን ልንገነባት ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ።ለመከፋፈልና የእኔ ለማለት ከመቸኮል ይልቅ የማያግባቡ ጉዳዮችን በመነጋገር መፍታትና መጓዝ እንደሚገባም ገልጸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በአለም አቀፍ ደረጃ ለ108ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ43ኛ ጊዜ እየተከበረ በሚገኘው አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ላይ ባደረጉት ንግግር ላይ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ መዲና ብሎም ሁሉን አቅ ፋና ተሸክማ የምትኖር ከተማ ናት።ሱዳን ካርቱም በርካታ ኢትዮጵያዊያንን ፣ ኬንያ ናይሮቢም በርካታ ሶማሌያዊያንን ይዘው ይኖራሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ አበባም ለኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆን የመላ አፍሪካዊያን ማዕከል መሆኗን ጠቁመዋል።ይሁንና ሁሉን ነገር ማሰባሰብ ሲቻል የሚያለያየን ከሆነ እንደዋዛ የምናፈርሰው፣ ሰብስበን የማንገነባውና ለትውልድ ዕዳ የምንጥል መሆኑን መገንዘብ ግድ ይላል ብለዋል።በመሆኑም ባፈረስነውም ልክ የማንገነባውና ለትውልድ ዕዳ የምንጥል እንዳንሆን ኢትዮጵያ በእናት እንደምትጠራው ሁሉ እናቶች ልጆቻቸው በትጋት እንዲጠብቋት በትጋት እንዲሰሩም ጠይቀዋል።“ኢትዮጵያዊያን እኔስ በአገሬ እንኳን ሰው ወፍ አላምዳለሁ” እንዲሉ የወፉ ይቅርብንና የራሳችን ወገን የሆነውን ኢትዮጵያዊ ማለማመድ የተሻለ ነው ሲሉም ተናግረዋል።ማንኛውም ሰላም ወዳድ ኢትዮጵያዊ የጎረቤቱን ሰላምና አብሮነት ልክ እንደራሱ ጉዳይ ማሰብና መስራት ይኖርበታል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድል ብቻ የመጋራትና ሽንፈትን የመሸሽ አባዜ እንዲወገድ ልጆችን በተገቢው መንገድ ማስተማር ያስፈልጋል ነው ያሉት።በዚህም ለመከፋፈልና የእኔ ለማለት ከመቸኮል ይልቅ የማያግባቡ ጉዳዮችን በመነጋገር መጓዝ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።በወጣትነት ዘመን እንዳለው ጀግንነት ማስፈራራት ብቻ ሳይሆን በአዛውንትነት ዘመን የሚመጣውን ቁጭትና ጸጸት ታሳቢ አድርገን ለጦርነትና ወንድምን ለመግፋት ያለንን ጉልበት ለሰላም፣ ለአንድነትና አብሮ ለመኖር መጠቀም ይኖርብናልም ብለዋል። (ኢዜአ) ", "passage_id": "286cc254ca9d7634226c7401eaff8639" } ]
5abe410f60a6f17e83454c55ccf460b6
eec78e643fb6f1c77aeb6a271955baf0
የፀረ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ መድኃኒት ከቅዱሳን መጻህፍት አስተምህሮ አኳያ
አስመረት ብስራትበሃይማኖት አባቶች ፀሎት የተከፈተው ጉባኤ እጅግ መከባበር የሞላበት ነበር። በፀረ ኤች አይቪ መድሀኒት ላይ አተኩሮ የኤች፣አይ.ቪ ታካሚዎች ህክምናቸውን በመውሰድ እንዳያቋርጡ ለማድረግ የተከናወነው የቅስቀሳ መድረክ የተለያዩ ታላላቅ መንፈሳዊ አባቶች፤ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፤ የሰራተኛና የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኝባቸው ሰዎችና ሌሎች ተሳታፊዎች ተገኝተውበት ነበር።የጉባኤውን መጀመር በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የጀመሩት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሀፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ፤ በሀገራችን የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሚቻለው ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኝ ሰዎች የህክምና ክትትላቸውን በአግባቡ ማከናወን እንዲችሉ ሲደረግ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አዲስ እያንሰራራ ያለው የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ ስርጭትን ለማቆም በሃይማኖት ሰበብ መድሀኒታቸውን የሚያቋርጡ ህሙማን ከዚህ ተግባር መቆጠብ እንደሚኖርባቸው አስረድተዋል።ኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉት አቶ መኮንን አለሙ በበኩላቸው፤ ከፀበል፣ ከዱአና ከፀሎት ጎን ለጎን መድሀኒቱን መውሰድ ያለምክንያት የሚጠፋውን የቫይረሱ ተጠቂዎችን ህይወት ሊታደግ እንደሚችል አስረድተዋል። ከሃይማኖት አባቶች ጋር የሚደረግ ግንኙነት የመንፈስ ጥንካሬን እንደሚያጎናፅፍ በመጥቀስም፤ መንፈሳዊውንም ሆነ ዘመናዊውን ህክምና ጎን ለጎን ማስኬድ አዲስ ከቫይረሱ ጋር የሚወለዱ ልጆች እንዳይኖሩ ማድረግ እንደሚያስችል ገልፀዋል። ቀደም ሲል የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር የሃይማኖት አባቶች አስተዋፅኦ የላቀ መሆኑን ያስታወሱት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በበኩላቸው፤ አሁንም ቢሆን በመቀዛቀዝ ላይ ያለው ኤች.አይ.ቪ ቫይረስን የተመለከተ ንቅናቄ አሁንም በሃይማኖት አባቶች አስተምሮት ሊደገፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። በሀገራችን ከ667ሺ በላይ ሰዎች በደማቸው ውስጥ ቫይረሱ መኖሩን በመጠቆም፤ በሁሉም ህብረተሰብ የጋራ ርብርብ መጥቶ የነበረው የአመለካከት ለውጥ ወደኋላ እንዳይመለስ የሃይማኖት አባቶች አስተምሮአቸውን አጠናክረው መቀጠል የሚገባቸው መሆኑን ጠቁመዋል።ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትሪያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እንዳሉት ደግሞ፤ ለመድሀኒት ሰሪዎች ጥበብን የሰጠው ፈጣሪ በመሆኑ መድሀኒትን መውሰድ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ አይከለክልም። የሰው ልጅም በምድር ኖሮ ለማለፍ እስከተፈጠረ ድረስ በህይወቱ መቀለድ የለበትም። በመሆኑም ፀበሉንም እምነቱንም ፀሎቱንም ሳያቆሙ መድሀኒት በመውሰድ እራሳቸውን ከከፋ ህመም መጠበቅ የሚገባቸው መሆኑን ያሳሰቡት ብፁዕ አቡነ ማትያስ፤ በእምነት እያሳበቡ መድሀኒት ማቆም ራስን ከመግደል የማይተናነስ መሆኑን አስረድተዋል። ፈጣሪ ከፈጠራቸው ተክሎች የተፈጠሩ መድሀኒቶችን አልውጥም ማለትም በፍፁም ከመንፈሳዊ አስተምህሮት ውጪ ነው ብለዋል።የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር እንድሪስ በበኩላቸው፤ የሰው ልጅ በቅድሚያ በበሽታ እንዳይጠቃ መጠንቀቅ እንዳለበት በመግለጽ፤ በበሽታ ከተያዘ በኋላ መድሀኒት አልወስድም ማለት ግን የእስልምና ሃይማኖት አስተምህሮ የማይደግፈው ተግባር መሆኑን አስረድተዋል። ህመም የመጣው ከፈጣሪ ማርከሻ መድሀኒቱም የሚገኘው በፈጣሪ ፍቃድ በመሆኑ የሃይማኖታዊ ስርአቶችን ከማከናወን ጎን ለጎን መድሀኒቶቻቸውን በአግባቡ መውሰድ የሚገባቸው መሆኑን አሳስበዋል።̋ካለ እርጅና ሞት በስተቀር፤ አላህ መድሀኒት የሌለው በሽታ አልፈጠረም፤” ያሉት ሀጂ ኡመር፤ ጥበቡን ሰጥቷቸው በቅንነት ሊረዱን የመጡ የህክምና ባለሙያዎችን ትዕዛዝ አለመተግበር ተገቢ አለመሆኑን ተናግረዋል። ብፁእ ካርዲናል ብርሀነ ኢየሱስ ሱራፌል ሊቀጳጳስ ዘካቶሊካውያን የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዚዳንት በበኩላቸው፤ በተወካያቸው በኩል ባስተላለፉት መልእክት፤ የሳይንስ ግኝት የፈጣሪ ፀጋ በመሆኑ መድሀኒቶች በምንም ሁኔታ ከሃይማኖታዊ ስርአት ጋር የማይጋጭ መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍሎች የተለያዩ መድሀኒቶችን መጠቀም መፈቀዱን አስታውሰው፤ ከሃይማኖት አባቶች ጋር የሚከናወኑ መንፈሳዊ ተግባራት ለስነልቦና እጅግ በጣም ጠቃሚ በመሆኑ ከመድሀኒቱ ጎን ለጎን እምነታዊ ተግባራትን መፈፀም ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል።በጉባኤው ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉ ሰባት የተለያዩ ሃይማኖቶች አባቶችም፤ መድሀኒት ማቋረጥ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ አለመሆኑን አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37933
[ { "passage": "በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው የማህጸን በር ካንሰርና ኤችአይቪ/ኤድስ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ እንደተገለጸው ከ90 በመቶ በላይ ለሚሆኑና ዕድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ዓመት ላሉ ሴት ታዳጊዎች ከማህጸን በር ካንሰር ጋር በተያያዘ ክትባት ተሰጥቷል፡፡   በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ኤችአይቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ገብረመድህን በሀገሪቱ የኤችአይቪ/ኤድስ ጉዳይ አሁን ላይ እየተረሳ መምጣቱን ገልጸው፣ ይህን መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ሊበራከቱ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡“ኑ ለሀገራችን ኢትዮጵያ ወጣት ሴት ተማሪዎችን እናፍራ” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው መድረክ ላይ የጡት ካንሰርና የማህጸን በር ካንሰር በኢትዮጵያ ብዙ ሴቶችን እንደሚያጠቃ የተገለጸ ሲሆን፣ ከ20 አመት በታች ያሉ ሴት ልጆችን የሚያጠቃውን የማህጸን በር ካንሰር አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻልና በጊዜ ከተደረሰበት በቀላሉ ሊታከም እንደሚችል ተገልጿል፡፡የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ይህን መሰል የግንዛቤ መድረክ መዘጋጀቱ በህብረተሰቡ ዘንድ የተሻለ ግንዛቤ በመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመው፣ ውይይቱ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባልም ብለዋል፡፡     ", "passage_id": "7e61ee7fb921b9cfbd3474ae5b299424" }, { "passage": " ሃያኛው የዓለም የኤድስ ጉባዔ ትናንት፣ ዕሁድ - ሐምሌ 13/2006 ዓ.ም ሲከፈት ግዙፍ የተባሉ ግቦችን አስቀምጧል፡፡ አንዱም እጅግ የገዘፈ መድረሻ በመጭዎቹ 15 ዓመታት ውስጥ ኤችአይቪን ከገፀ-ምድር ማጥፋት ነው፡፡ዓለምአቀፉ ጉባኤ ሜልቦርን - አውስትራሊያ ላይ ሲከፈት የበረታ የኀዘን ድባብ ሰፍኖበት ነበር፡፡ ባለፈው ሣምንት ውስጥ ለጉባዔው ለመድረስ ከሆላንድ ተነስተው ወደ ኳላ ለምፑር ሲጓዙ የነበሩ ስድስት ከፍተኛ ተመራማሪዎችና ኤክስፐርቶች ምሥራቅ ዩክሬን ውስጥ ከምድር በተተኮሰ የሚሳይል አረር ተመትቶ በወደቀው የማሌዥያ የመንገደኞች አይሮፕላን ውስጥ ነበሩ፡፡እስከ ፊታችን ዐርብ በሚዘልቀው የዘንድሮው ጉባዔ ላይ አችአይቪን ለማምከንና መተላለፉን ለማስቆም፣ እንዲሁም ኤድስን ለማከምና ከእንግዲህ ማንም በኤድስ ምክንያት እንዳይሞት፣ ማንም ሕፃን ሲወለድ ከኤችአይቪ ነፃ ሆኖ እንዲወለድ ለማድረግ የተያዙትን የሣይንስ ጥረቶች፣ ኤችአይቪ በዓለም ዙሪያ ቤተሰቦችንና ማኅበረሰቦችን እንዴት እንደጎዳ እንደሆነና ና እየጎዳ ስላለባቸው ሁኔታዎተ ሰፋፊ ፍተሻዎችና ጥልቀት ያላቸው ውይይቶች በየመድረኩ ይካሄዳሉ፡፡ኤችአይቪ/ኤድስ ባለፉት ሰላሣ ዓመታት ውስጥ ወደ አርባ ሚሊየን የሚሆን ሰው በዓለም ዙሪያ ገድሏል፡፡ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡", "passage_id": "ce571514fa5b1139793ceebe43ec60e7" }, { "passage": "የካንሰር በሽታም ተጠቂ የሆነው የለንደን ከተማ ነዋሪ የሙከራ ህክምናውን ለ18 ወራት ሲከታተል የነበረ ሲሆን በሰውነቱ ውስጥ ያለው ደም ከቫይረሱ ነጻ ስለሆነ የኤችአይቪ መድሃኒቶቹን መውሰድ አቁሟል።\n\nተመራማሪዎቹ እነደሚሉት ግን ሙሉ በሙሉ ከቫይረሱ ተፈውሷል ለማት ጊዜው ገና ነው ብለዋል።\n\n• በኢትዮጵያ 76 በመቶ የሚሆኑት ወጣት ሴቶች ስለ ኤችአይቪ እውቀት የላቸውም ተባለ\n\n• ኤች አይ ቪን የሚከላከለው መድሃኒት ተስፋ ሰጪ ነው ተባለ\n\nየዘርፉ ባለሙያዎች በህክምናው ውጤት መደመማቸውን ቢገልጹም ተመራማሪዎቹ ቫይረሱን ከደም ውስጥ ለማጥፋት የተጠቀሙት መንገድ ሁሉም ተጠቂዎች ላይ ተግባራዊ መሆን የሚችል ባለመሆኑ ተጨማሪ ስራ ይጠይቃል ብለዋል።\n\nለወደፊቱም ለቫይረሱ ፈውስ ለማግኘት ትልቅ መነሻ ሊሆን እንደሚችልና ለብዙ ዓመታት ሲጨነቁ ለነበሩ ተጠቂዎች ተስፋ ሰጪ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።\n\nበሙከራ ህክምናው ላይ የለንደን ኮሌጅ ዩኒቨርሲቲ፣ የለንደን ኢምፔሪያል ዩኒቨርሲቲ፣ የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲና የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማዎች ተሳትፎ ማድረጋቸው ታውቋል።\n\nበዚህ አይነት መንገድ ቫይረሱን ከደም ውስጥ የማጥፋት ስራ ሲከናወን ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።\n\nየዛሬ አስር ዓመት አንድ ጀርመናዊ የቫይረሱ ተጠቂ ተፈጥሮአዊ የመከላከል ብቃት ካለው በጎ ፈቃደኛ በተገኘ የመቅኔ (ቦን ማሮው) ንቅለ ተከላ ተደርጎለት ነጻ መሆን መቻሉ ይታወሳል።\n\nምንም እንኳን ይሄኛው ግኝት አስደሳች ቢሆንም በሚሊዮን ለሚቆጠሩት የዓለማችን የኤች አይቪ ተጠቂዎች ተደራሽነቱ አጠራጣሪ ነው። የህክምና ሙከራው ከሌሎቹ ለየት ባለ መልኩ ለካንሰር ህክምና የሚደረጉ ስርአቶችን ይከተላል።\n\n• ስለኤች አይ ቪ /ኤድስ የሚነገሩ 8 የተሳሳቱ አመለካከቶች\n\nአሁን ያሉት የኤችአይቪ ማዳከሚያ መድሃኒቶች ተጠቂዎቹ ጤናማና ረጅም እድሜ እንዲኖሩ የሚያስችሏቸው ስለሆኑ ይሄኛውን መንገድ እንደ ብቸና አማራጭ አድርጎ ለመወሰድ ከበድ ያደርገዋል።\n\nሰውነታችን እራሱን ከበሽታ እንዴት እንደሚከላከል በእርግጠኝት ለመረዳትና ለወደፊት ፍቱን መድሃኒቶችን ለማግኘት ግን ይሄኛው ህክምና ፈር ቀዳጅ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። \n\nበለንደን ኢምፔሪያል ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑትና በጥናቱ የተሳተፉት ፕሮፌሰር ኤድዋርዶ ኦሊቬራ እንደሚገልጹት በህክምናው ሂደት ''ሊምፎማ' የተሰኘውን የካንሰር አይነት ለማከም የሚጠቀሙበትን መንገድ ተግባራዊ ስላደረጉ ሂደቱን አስቸጋሪ ያደርገዋል።\n\n''የህክምና መንገዱ በራሱ መርዛማ የሆኑ ነገሮችን ስለሚያካትትና ለረዥም ጊዜ ስለሚካሄድ ተግባራዊነቱን ትያቄ ውስጥ ይከተዋል። ነገር ግን ወዴት መሄድ እንዳለብን ትክለኛ አቅጣጫ ጠቋሚ ነው።'' \n\n ", "passage_id": "57c770f2b6d98b0cb46e9ff8ba89de19" }, { "passage": "የወባ መድኃኒትን ለኮቪድ 19 ሕክምና ማዋል ይቻላል? “ምን ይቀርብናል?” ይላሉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ። “የለም፤ ፍቱን ስለመሆኑ ማረጋገጫ የለንም” የሚሉም አሉ _ ከሕክምናውና ከምርምሩ ዓለም ቤተሰቦች መካከል ያሉ።ክትባቱን ለማድረስ የሚማስኑ፤ መድኃኒት ከባሕላዊውም ከዘመናዊውም አድርገን እንቀምማለን የሚሉም ጥቂት አይደሉም፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ።ከሁሉም ወገኖች እየተነሣ ያለውን ንግግር ሰሎሞን አባተ በተከታዩ ቅንብር አካትቷል።።\n", "passage_id": "17d3ee6515659813f4c4ed75edef00a7" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የኤች አይ ቪ ህሙማን መድሃኒት አቅርቦት እንዳልተቋረጠ የፌዴራል ኤች አይቪ ኤድስ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ፅህፈት ቤት ገለጸ። \nየፌዴራል ኤች አይቪ ኤድስ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ፅህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል በትረ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ በኮሮና ቫይረስ ተፅዕኖ ምክንያት ኤች አይ ቪ በደማቸው የሚገኙ የህብረተሰቡ ክፍሎች መደኃኒታቸውን በአካባቢያቸው ከሚገኝ የጤና ተቋም መውሰድ እንዲችሉ የሚያግዝ ስራ እየተሰራ ነው። \nከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የኤች አይቪ ኤድስ መድሃኒት አቅርቦት የራሱ የሆነ ተፅእኖ ማሳደሩ የማይቀር መሆኑን የሚገልጸት አቶ ዳንኤል ፤ ጽህፈት ቤቱ ችግሩን ለመቅረፍ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አመልክተዋል። \nሰዎች በትራንስፖርት ችግር ምክንያት ከቦታ ቦታ\n መንቀሳቀስ የማይችሉበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ኤች አይ ቪ በደማቸው የሚገኙ የህብረተሰቡ ክፍሎች መድሃኒታቸውን ከአካባቢቸው ከሚገኝ የጤና ተቋም መውሰድ እንዲችሉ የሚያግዝ አሰራር መዘርጋት አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል። መድሃኒት ማቋረጥ የሚያስከትለው ተፅዕኖ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን ማከናወን ሌላው ትኩረት የተሰጠው ስራ መሆኑን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት አዲስ የኤች አይ ቪ ቫይረስ በደማቸው ለሚገኝባቸው ዜጎች የድጋፍ እና የእንክብካቤ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። መደበኛ ስራዎችም በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መከወን እንዲችሉ የሚያግዝ መመሪያዎችን በማዘጋጀት ለሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በመላክ በመመሪያው መሰረት ወደትግበራ እንዲገቡ የማድረግ ስራ እየተሰራ ገልጸዋል። \nበተለያዩ አካባቢዎች ሰዎች መድሃኒታቸውን በአግባቡ የማይወስዱበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል የሚናገሩት አቶ ዳንኤል ፤ አሁን ላይ እንደ ሀገር የተፈጠረ ችግር የሌለ መሆኑን አመልክተዋል። ይህም ሆኖ ግን ቅሬታዎች መኖራቸውን አመልክተዋል።\n ከዚህ በፊት ለኤች አይ ቪ እና ሌሎች አገልግሎቶች አገልግሎት ይሰጡ የነበረ ሆስፒታሎች ሙሉ በሙሉ ለኮቪድ 19 መከላከል ስራ ሲታጠፉ ከሆስፒታሎቹ መድሃኒት የሚወስዱ ኤች አይ ቪ በደማቸው የሚገኝ የህብረተሰቡ ክፍሎች ግራ የመጋባትና የት ሄደን መድሃኒት እንወስዳለን ብሎ የመጨነቅ ሁኔታ መስተዋሉን ጠቁመዋል። \nበአዲስ አባባና በክልሎች የሚገኙ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኙ ዜጎች ባቅራቢያቸው መድሃኒቱን የሚያገኙበትን አሰራር ለመዘርጋት የሚያስችሉ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን አመልክተዋል። በዚህ መሃል መድሃኒት መውሰድ ሳይችሉ የቀሩ ወገኖች ይኖራሉ የሚል ግምት ያለ መሆኑንም ገልጸዋል። \nመድሃኒቱን ከአካባቢያቸው ከሚገኝ የጤና ተቋም የሚወስዱ ኤች አይ ቪ በደማቸው የሚገኝ የህብረተሰቡ ክፍሎች መኖራቸውን ያመለከቱት አቶ ዳንኤል ፤ ይህ ደግሞ የሚሆነው መገለል እና መድሎን በመፍራት መሆኑን አፅኖት ሰጥተው ተናግረዋል። \nለምሳሌ የአዲስ አባባ ነዋሪ ሆኖ ሞጆ ሂዶ መድሃኒት የሚወስድ የሞጆ ነዋሪ ሆኖ እያለ ከአዳማ መድሃኒት\n የሚወስድ መኖራቸውን አመልክተው ፣ እነዚህ ወገኖች ሲጀመር መድሃኒታቸውን በዚህ መንገድ መውሰድ ትክክል አይደለም ብለዋል። ስለዚህ እኚህ ሰዎች አሁን ላይ ካለው የትራንስፖርት ችግር ጋር በተያያዘ መድሃኒታቸውን ሂደው ለመውሰድ የመቸገር ነገር መኖሩን ጠቁመው፤ በዚህ ምክንያት አንዳንድ ቦታዎች ላይ መድሃኒቱን የማቋረጥ ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች ስለመኖራቸው በዳሰሳ ጥናት የተረጋገጠ መሆኑን አቶ ዳንኤል ገልጸዋል ። \nእነኝህ የህብረተሰብ ክፍሎችን መድሃኒታቸውን በአግባቡ ከአካባቢያቸው ከሚገኝ የህክምና ተቋም መውሰድ እንዲችሉ በሚዲያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመው ፤ ለዚህ ሲባል የተዋቀሩ የተለያዩ የውይይት መድረኮች መኖራቸውን አመልክተዋል። ክልሎችም ሆኑ የከተማ አስተዳደሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ የሚፈጠረውን ተፅዕኖ ለመቀነስ የሁሉም ባለድረሻ አካላት ርብርብ አስፈላጊ እንደሆነም አመልክተዋል።\nአዲስ ዘመን ሰኔ 15/2012\nአሸብር ሀይሉ", "passage_id": "2918a9af228c1ba98769abc627091459" } ]
4f0ec72203684303c6cb02bb116a8949
f975224814eb85aad08a27c995817262
አልጄሪያና የ2020 የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ዝግጅት
 በቀጣዩ ሰኔ ወር የአፍሪካ ምርጥ አትሌቶች በሰሜን አፍሪካዊቷ አገር አልጄሪያ ለመፋለም ቀጠሮ ይዘዋል።መዲናዋ አልጄርስም በሃያ ሁለተኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአህጉሪቱ ኮከብ አትሌቶችን ለመቀበል ከወዲሁ ዝግጅቷን እያገባደደች እንደምትገኝ አሳውቃለች።የአፍሪካውያን አትሌቶች ከቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አስቀድሞ በቻምፒዮናው ለኦሊምፒክ የሚያበቃቸውን ሰዓት ለማሟላት ብርቱ ፉክክር የሚያደርጉበት ትልቅ አጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል። የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽንም ይህ ቻምፒዮና የተሳካ እንዲሆን ከአልጄሪያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር እየሰራ እንደሚገኝ አሳውቋል፡፡‹‹ ለቻምፒዮናው በሚደረገው ዝግጅት ረክተናል፣ ነገር ግን ይህ ለኛ አዲስ አይደለም›› በማለት ሰሞኑን ለመገናኛ ብዙሃን የተናገሩት የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ዳይሬክተር ላሚን ፋቲ የአልጄሪያን ዝግጅት ለመገምገም ወደ ስፍራው ያቀናው ቡድን ነገሮች በጥሩ መልኩ እየሄዱ እንደሚገኙ ማረጋገጡን አስረድተዋል።ለዚህም አልጄሪያ የሰውሃብትና አስፈላጊው ቁሳቁስ በበቂ ሁኔታ ያላት አገር መሆኗ ዝግጅቱን ቀላል እንዳደረገው ተናግረዋል። እ.ኤ.አ ከሰኔ 24 እስከ 28 በሚካሄደው ቻምፒዮና ውድድሮችን የሚያስተናግደው ‹ጁላይ 5› ስቴድየም እድሳትና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እንዲካተቱበት ተደርጎ ሰማንያ ሺ ተመልካች እንዲይዝ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ነው።እኤአ በ1972 በቀድሞው የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት ሁአሪ ቡሜዴን ተመርቆ ስራ የጀመረው ስቴድየም በርካታ ታላቅ ውድድሮችን የማስተናገድ ልምድ አለው።እኤአ በ1975 በሜድትራኒያን ጨዋታዎች ይህ ስቴድየም የአትሌቲክስ ውድድሮችን በዋናነት ማስተናገድ ችሏል።እኤአ 1978ና 2007 የመላ አፍሪካ ጨዋታዎችን ከማስተናገዱ በተጨማሪ 2000 ላይ የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻፒዮናን ማስተናገድ እንደቻለ ይታወሳል። የኮንፌዴሬሽኑ ዳይሬክተር ፋቲ ባለፈው ወር ለአልጄሪያ መገናኛ ብዙሃን ‹‹የስቴድየሙ እድሳት ገና ሳይጠናቀቅ ገምጋሚ ቡድኑ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች ረክቷል፣ በቀጣይ በሚከናወኑ ስራዎች ደግሞ የተሻለ ነገር እንደምናይ ተስፋ አለን›› ማለታቸው ይታወቃል።የአልጅሪያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ጋር በጋራ በመሆን አትሌቶች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎችም በቻምፒዮናው ለመታደም ወደ ስፍራው ለሚያቀኑ አካላት የቪዛና የትራንስፖርት አገልግሎቶችን ለማቀላጠፍ በርካታ ስራዎችን ከወዲሁ እያከናወኑ እንደሚገኙ አሳውቀዋል።ውድድሩ በበርካታ የአፍሪካ አገራት የቀጥታ የቴሌዥን ስርጭት ሽፋን እንዲያገኝም የተለያዩ ስራዎች ተሰርተዋል። በቻምፒዮናው የአትሌቶች አበረታች ንጥረ ነገሮች ተጠቃሚነት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲኖር ከወዲሁ ዝግጅት መደረጉም ታውቋል።አልጄሪያ ይህን ቻምፒዮና ስታስተናግድ የዘንድሮው ሦስተኛዋ ይሆናል።ከዚህ ቀደም እኤአ በ1988 በአናባ ከተማ ቻምፒናውን ያስተናገደች ሲሆን ከሃያ ዓመት በፊት 2000 ላይ በአልጄርስ ቻምፒዮናውን ማስተናገድ ችላለች። በ1988 ቻምፒዮና አልጄሪያ በአስራ አንድ የወርቅ ሜዳሊያ ቀዳሚ ሆና ካጠናቀቀችው ናይጄሪያ በአንድ የወርቅ ሜዳሊያ ዝቅ ብላ በሁለተኛነት ማጠናቀቋ ይታወቃል።ከአስራ ሁለት ዓመታት በኋላ 2000 ላይ ባስተናገደችው ቻምፒዮና ግን አስራ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎች በመሰብሰብ ቀዳሚ ሆና አጠናቃለች።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 22/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=25009
[ { "passage": "በሚቀጥለው ዓመት ኬንያ ለምታስተናግደው የአፍሪካ ሃገራት ቻምፒዮና (ቻን) ለማለፍ የሚደረጉ የማጨረሻ ማጣሪያ ዙር ጨዋታዎች ቅዳሜ ተጀምረዋል፡፡ ከምስራቅ እና መካከለኛ አፍሪካ ዞን ሶስት ሃገራት (አዘጋጇን ኬንያ ጨምሮ) በውድድሩ ላይ ተሳትፎ ያደረጋሉ፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ 10፡00 ሰዓት ላይ ሱዳንን ሀዋሳ ላይ ታስተናግዳለች፡፡ የሱዳን ብሄራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ላይ ካደረገ በኃላ ቡድኑን ለረጅም ግዜያት ያክል የመሩት መሃመድ አብደላ አህመድ (በቅፅል ስማቸው ማዝዳ) ከሶከር ኢትዮጵያ በቡድናቸው ዝግጅት እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ቆይታ አድርገዋል፡፡ስለዝግጅት\nይህ በሃገር ውስጥ ሊግ ብቻ ለሚጫወቱ ተጫዋቾች የተዘጋጀ ውድድር ነው፡፡ ለዚህም ለውድድሩ እያዘጋጀን ያለነው ሙሉ ለሙሉ አዲስ ቡድን ነው፡፡ ይህንን ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጀምሮ ማዘጋጀታችንን ጀምረናል፡፡ ከዛም ከቡሩንዲ ጋር ተጫውተናል፡፡ እንዲሁም ከፊታችን ላለብን ጨዋታ ሩዋንዳን በአቋም መለኪያ ጨዋታ ገጥመናል፡፡ አሁን ሀዋሳ እንገኛለን፡፡ ጨዋታው ከባድ እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ቢሆንም ተጫዋቾቻችን የተሻለ አቋም ላይ ይገኛሉ ብዬ አስባለው፡፡ከታላላቆቹ አል ሂላል እና ኤል ሜሪክ የተመረጡ ተጫዋቾች ቁጥር ማነስይህ ምንም ለውጥ አይደለም ፤ የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡ ሁልግዜም ምርጫችንን መሰረት ያደረገው በሚሆኑ ዝግጁ በሆኑ ተጫዋቾች ላይ ነው፡፡ ከአካል ዝግጁነት አንፃር ብሄራዊ ቡድን ላይ አይደለም ተጫዋቾች በዚህ ረገድ ዝግጅት የሚጀምሩት ስለዚህም የተሻሉ የምንላቸውን መርጠናል፡፡ ስለዚህም በሊጉ ጥሩ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተጫዋቾችን ይዘናል፤ ከዚህ በፊት በነበረው ጨዋታም ጥሩ ነበሩ፡፡ እኛ ትኩረት ያደረግው አዲስ ቡድን መገንባት ላይ ነው፡፡ የዚህ ቡድን አማካይ እድሜ 23 ዓመት ነው፡፡ አብዛኞቹ ከኦሎምፒክ (ከ23 ዓመታ በታች) ቡድናችን ነው የመጡት፡፡የሱዳን ብሄራዊ ቡድን በማጣሪያ ጨዋታዎች እያሳየ ስለሚገኘው ደካማ አቋም እና ወቅታዊ የሃገሪቱ እግርኳስ ሁኔታበአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ አሁን ላይ አንድ ጨዋታ ብቻ የተጫወትነው፡፡ 24 ቡድን ስለሚሳተፍ እድላችን ሰፊ ነው፡፡ አሁን ላይ ከዚህ በፊት ከነበሩት ቡድኖች እየተሻልን ነው፡፡ ማዳጋስካርን በምንገጥምበት ወቅት ከፊፋ ቅጣት ጋር በተያያዘም ከፍተኛ ችግሮች ነበሩብን፡፡ ተጫዋቾችን ለመሰብሰብ እራሱ ችግሮችን ማለፍ ነበረብን፡፡ ለማዳጋስካሩ ጨዋታ ሁለት የልምምድ ግዜያት ብቻ ነበሩን፡፡ ከእግርኳስ ፍልስፍና አንፃር አዲስ ቡድን ይዘህ ሁለት የልምምድ ግዜያት ማለት ምን እንደሆነ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ የአቋም መለኪያ ጨዋታም አላደረግንም ግን ይህንን ችግር እንቀበላለን፡፡ አሁን ላይ የቡድኑ ዝግጅት የተሳካ እንዲሆን የሚሰራ ኮሚቴ አለ፡፡ አሁን በፊፋ ያለን ደረጃ በጣም መጥፎ ነው፡፡ ሁለት ዓመት ሙሉ በዚህ ስራ ላይ ነኝ ግን በነዚህ አመታት ውስጥ እምብዛም የአቋም መለኪያ ጨዋታ አላደረግንም፡፡ አሁን ጥሩ ቡድን አለን፡፡ ሊጉም ጥሩ እየሆነ ነው፡፡ ሁለቱ ታላላቅ ክለቦቻችን (ሂላል እና ሜሪክ) እራሱ በሊጉ እየተፈተኑ ነው፡፡ አዳዲስ ተፎካካሪ ቡድኖች እየመጡ ይገኛሉ፡፡ በተለይ ከኮንፌድሬሽን ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ላይ ከቲፒ ማዜምቤ የሚጫወተው ሂላል ኦባያድን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከዚሁ ቡድን 6 ተጫዋቾችን ይዘናል፡፡ ይህ ለሃገሪቱ እግርኳስ አዲስ ነው፤ ከሜሪክ እና ሂላል ውጪ ያለ ቡድን ብዙ ተጫዋቾችን ለብሄራዊ ቡድን ሲያስመርጥ፡፡ ሂላል እና ሜሪክ ሁለት ሁለት ተጫዋቾችን ብቻ ያስመረጡት፡፡ ሃገራችን በችሎታ በኩል ምንግዜም አትሰቃይም፡፡ መጫወት የሚችሉ ልጆች አሉን፡፡ ችግሩ ዝግጅት ላይ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የፋይናንስ አቅም ሊኖርህ ይገባል፡፡ለረጅም ግዜ በብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝነት ስለመቆየታቸውከዚህ በፊት የነበራችሁ አሰልጣኝ (ሰውነት ቢሻው) ጥሩ ነገሮችን ሲሰራ ነበር በተመሳሳይም ረዘም ላለ ግዜ ቆይቷል፡፡ ጥሩ ጓደኛሞች ነን፡፡ በሃገራችን ጥሩ የሆነ የእግርኳስ አሰልጣኝ ካለ ረጅም ግዜ መስራት ይችላል፡፡ ይህ ምንም ሚስጥር አይደለም፡፡ ልምድ አለኝ እንዲሁም በምመርጣቸው ተጫዋቾች በአብዛኛው ደጋፊው ከእኔ ጋር ይስማማል፤ በምርጫ ላይም አልቸገርም በዚህ ላይ ይህ ሃገር በሜሪክ እና ሂላል ባላንጣናት የተከፈለ ሃገር በመሆኑ ሁልግዜም ቴክቲካል የሆኑ አስተያየቶችን የሚሰጡ በርካታ ደጋፊዎች ያሉበት ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ረጅም ግዜ ለመቆየት ጠንካራ መሆንን ይፈልጋል፡፡", "passage_id": "326ea5cd249b389bb387ccf07953a05b" }, { "passage": "እአአ 1965 መነሻውን በኮንጎ ብራዛቪል አደረገ፤ ለግማሽ ምዕተ ዓመትም ሃገራት እየተቀባበሉት ከዛሬ ደርሷል። ተረኛ አዘጋጅ የሆነችው የሞሮኮዋ ራባትም ከዛሬ ጀምሮ ከ54ቱ የአፍሪካ ሃገራት የተወጣጡትን 6ሺ አትሌቶች በ26 የስፖርት ዓይነቶች ለ12 ቀናት ታፋልማለች ። የመክፈቻ መርሐ ግብሩም በንጉሥ መሃመድ ስድስተኛ ስታዲየም ይካሄዳል። ሞሮኮ ውድድሮቹን በሰባት ከተሞቿ ያሰናዳች ሲሆን፤ ራባት፣ ካሳብላንካ፣ ሳሌ፣ ቴማራ፣ ኬህሚሴት፣ ሞሃመዲያ እና ኤል ጃዲድ ደግሞ ከተሞቹ ናቸው። የውሃ ዳር ቮሊቦል እና እግር ኳስ ውድድራቸውን ቀድመው ሲጀምሩ፤ የጁዶ ስፖርት ግን ከትናንት በስቲያ እና ትናንት በተካሄዱ ውድድሮች ማጠቃለያውን አግኝቷል። ከነገ ጀምሮም ሌሎች ስ ፖርቶች መካሄድ ይጀምራሉ። ኦሊምፒክ ከመካሄዱ ከአንድ ዓመት በፊት የሚካሄደው ይህ ውድድር የአህጉራት ኦሊምፒክ በመባል የሚታወቅ ሲሆን፤ ለታላቁ ውድድር እንደ አንድ የመምረጫ መስፈርት ያገለግላል። እአአ በ2020 የጃፓኗ ቶኪዮ በምታካሂደው ኦሊምፒክ ከመወዳደሪያ ስፖርቶች መካከል 18 በሚሆኑት የሚሳተፉ ስፖርተኞች በመላ አፍሪካ ጨዋታ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። ኢትዮጵያም በዚህ ውድድር ተሳታፊ ከሆኑት ሃገራት መካከል ስትገኝ፤ ልዑካን ቡድኗን ባሳለፍነው ሳምንት አጋማሽ ወደ ቦታው ሸኝታለች። በውድድሩ የምትካፈልባቸው ስፖርቶችም 13 ሲሆኑ፤ አትሌቲክስ፣ ብስክሌት፣ ቦክስ፣ ካራቴ፣ ወርልድ ቴኳንዶ፣ ቼስ፣ ክብደት ማንሳት፣ የውሃ ስፖርቶች፣ ጂምናስቲክ፣ ቅርጫት ኳስ፣ ባድሜንተን፣ ጠረጴዛ ቴኒስ እና ሜዳ ቴኒስ ናቸው፡፡ የብሄራዊ ቡድን አባላትም በእነዚህ መስኮች ዝግጅታቸውን አጠናቀው ለውጤት ተዘጋጅተዋል። ከእነዚህ ስፖርቶች መካከል ቼስ፣ ካራቴ እና ሦስት በሦስት ቅርጫት ኳስ ደግሞ ሃገሪቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በመድረኩ የምትሳተፍባቸው ስፖርቶች ናቸው። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር የደረጃ ሰንጠረዥ በ122 ሜዳሊያዎች ስምንተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ከእነዚህ መካከልም 39ኙ የወርቅ፣ 39ኙ የብር እንዲሁም 52 ቱ የነሐስ ሜዳሊያዎች ናቸው። ከአራት ዓመታት በፊት በኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ኬንያን በመከተል ስምንተኛ ሆና ያጠናቀቀች ሲሆን፤ 6 የወርቅ፣ 5 የብር እና 6 የነሐስ በጥቅሉ 17 ሜዳሊያዎችን ነበር ያስመዘገበችው።አዲስ\nዘመን\nነሐሴ 13/2011 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "84df15044beca08da7d37f6e01054bfb" }, { "passage": "የኢትዮጵያ\nእግር ኳስ ፌዴሬሽን በአገር ውስጥ ሊጎች የሚጫወቱ ተጫዋቾች ብቻ የሚሳተፉበትን የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮን ሺፕ /ቻን/ እኤአ በ2020 ለማስተናገድ ከካፍ ኃላፊነቱን ከተረከበ ዓመታት አልፈዋል። ፌዴሬሽኑ ለስድስተኛ ጊዜ የሚካሄደውን ውድድር ለማሰናዳት ለካፍ ሲያመለክት አገሪቱ ቀደም ሲል የአፍሪካ ዋንጫን በብቃት ማስተናገዷን ጠቅሷል፤ ይህ ብቻም አይደለም በየክልሉ የተገነቡትን እና እየተገነቡ ያሉትን ስታድየሞችና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በማስረጃነት በማቅረብም ፍላጎት ብቻም ሳይሆን አቅሙም እንዳለው ለማሳየት ሞክሯል። የካፍ\nፕሬዚዳንት ማዳጋስካራዊው አህመድ አህመድ ወደ ተመረጡባት ኢትዮጵያ ብቅ ባሉበት ወቅትም አገሪቱ በስፖርት መሰረተ ልማት በተለይ ለእግር ኳሱ እድገት ከፍተኛ ወጪ በመመደብ እያከናወነች የምትገኛቸው የተለያዩ ተግባራት በማድነቅ፤አህጉራዊ ውድድሮች የማዘጋጀት ፍላጎቷንም በስኬት የማድመቅ ተስፋ እንዳላት መናገራቸው ይታወሳል። በእርግጥም አገሪቱ የአፍሪካ ዋንጫን ጨምሮ ሌሎችም አህጉራዊ ውድድሮችን ለማስተናግድ ፅኑ ፍላጎት አላት።ይህን የማድረግ ፍላጎት ብቻ ሳይሆን አቅምም እንዳላት ለማሳየት ታዲያ ቻንን ለማዘጋጀት የተቀበለችውን አደራ በብቃት መወጣት ግድ ይላታል። ይሁንና ሀገሪቱ ለመስተንግዶ የምታደርገው ዝግጅት ሲፈተሽ ግን በቂ ፍጥነት እንደሌለው በገሃድ የሚታይ ሃቅ ነው።አሁንም ቢሆን ስራዎች በበቂ መልኩ ሲከወኑም አይታይም።ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር ብሄራዊ ኮሚቴ በማቋቋም የሚሰሩ ስራዎች ደካማ ሆነው ይስተዋላሉ። በእነዚህ\nምክንያቶችም የአገሪቱ የቻን ዋንጫ ዝግጅት በምን ዓይነት ቁመና ላይ እንደሚገኝ በቅጡ አይታወቅም።የመሰናዶ ዝግጅት ለመገምገም ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የካፍ ልዑካን ቡድንም፤መሰረታዊ ግንባታዎች እስከ ውድድሩ መቃረቢያ ወቅት መጠናቀቅእንዳለባቸው ማሳሰቡ ይታወሳል። ይሁንና\nአሁን ባለው የኢትዮጵያ ስቴዲየሞች የግንባታና መሰናዶ አካሔድ በተለይ በክልሎች የሚገኙና ግንባታቸው የተጀመሩ ስታዲየሞች የካፍን መስፈርት አሟልተው በወቅቱ ስለመድረሳቸው ማረጋገጫ ለማግኘት ከባድ ሆኗል።ከስታድየሞቹ የውጭ ገፅታም በላይ ውስጣዊ ሙሉነታቸው ከሙሉው ይልቅ ጎዶሎው ቀድሞ የሚታይ ነው።ይህ መሆኑም አገሪቱ አዘጋጅነቷን የመነጠቅ ዕጣ ፋንታ እንዳይደርስባት የሚሰጉ እንዲበራከቱ ምክንያት ሆኗል። በዚህ ረገድ አዲስ ዘመን ያነጋገራቸው የዘርፉ ባለሙያዎች በአንፃሩ፤አዘጋጅነቱን መነጠቅና አሳልፎ መስጠት ከሚያደርሰው ፖለቲካዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ኪሳራ ለመዳን ሊከናወኑስለሚገባቸው አብይት ተግባራት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የኮተቤ ሜትሮ ፖሊታንት ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስ መምህር አቶ ሲያምረኝ በርሄ የአህጉራዊ የእግር ኳስ ውድድሮችን ለማሰናዳት ጥያቄ ስታቀርብ የነበረችው ኢትዮጵያ፣ እንደ አፍሪካ ዋንጫ ያሉ ውድድሮችን ለማሰናዳት ቻንን በአግባቡ መጠቀም እንዳለበትና አቅሟን ማሳየት ይገባታል»ይላሉ። ይሁንና በአገር ውስጥ ሊጎች የሚጫወቱ ተጫዋቾች ብቻ የሚሳተፉበትን የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮን ሺፕ /ቻን/ ውድድር የሚሰጠው አመለካከት የተዛባ መሆኑን የሚያስገነዝቡት አቶ ሲያምረኝ፤ከሁሉም በላይ ውድድሩን ዝቅ አድርጎ የመመልከት ከፍተኛ የተሳሳተ አመለካከትመኖሩንም ይገልፃሉ። እንደ አቶ ሲያምረኝ ገለፃ፤ቻን ከአፍሪካ ታላላቅ የእግር ኳስ ውድድሮች አንዱና እውቅና ያለው ነው።በአገር ውስጥ ሊጎች የሚጫወቱ ተጫዋቾች ብቻ የሚሳተፉበት እንደመሆኑ ለወጣት የነገ ተተኪዎች እድል የሚፈጥርና ጎልተው እንዲታዩ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው።በአሁኑ ወቅትም የላቀ ትኩረት አግኝቷል። የምዕራባውያን መልማዮች አይን ማረፊያ ከሆነም ቆይቷል፡፡ «ውድድሩ በዚህ ረገድ የላቀ ግምት የሚሰጠው እንደመሆኑም አዘጋጅ አገራት፤የማስተናገድ እድል ሲያገኙ የሚጠቀሙት ፖለቲካዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትሩፋት ከፍተኛ ነው»የሚሉት አቶ ሲያምረኝ፥በውድድሩ የቆይታ ጊዜ የመላአፍሪካና ዓለም አይን በአገሪቱ ላይ እንደመሆኑ በገፅታ ግንባታ ረገድ የሚኖረው አበርክቶም የላቀ መሆኑንም ይገልጻሉ።በብሄራዊ\nቡድን ደረጃም ቢሆን፤ውድድሮችን በማስፋት በቂ ልምድ እንደሚያስገኝ ይናገራሉ፡፡ በስፖርት ቱሪዝሙም የሚገኘው ገቢም ለረጅም ዓመታት ተሰርቶ የማይገኝ ስለመሆኑ ያመላክታሉ። በስንት ተማጽኖ ተጠይቆ የሚገኝ አዘጋጅነት መነጠቅ የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያስቀርም አቶ ሲያምረኝ ያስገነዝባሉ፡፡ ‹‹መሰል ውድድሮችን ለማሰናዳት አሁን በእጅ የተያዘውን አጋጣሚ መጠቀሙ እንደ ቀላል ነገር መታየቱ መቆም ይኖርበታል፤ለመስተንግዶ ስኬት የሚመለከታቸው አካላት በተለይም ከመስተንግዶው ተጠቃሚ የሚሆኑ ባለሃብቶች የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸውም ይላሉ። ውድድሩን ለማስተናገድ ከሚቀረው ከአንድ ዓመት ያነሰ ጊዜ ውስጥ በመላ አገሪቱ የተገነቡ ዘመናዊ ስታዲየሞችና ለእንግዶች መስተንግዶ ግልጋሎት የሚሰጡ ግንባታዎን ማቀላጠፍን ጨምሮ አስፈላጊውን ዝግጅት መቋጨት እንደሚገባ ያስገነዝባሉ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስ መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ወንድሙ ታደሰ እንደሚሉት፤ውድድሩን ለማዘጋጀት መብቃት ከስፖርቱ ጨዋታ ባሻገር በተለይ የአገር ገፅታን በመገንባት ፖለቲካዊ፤ ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦው ከፍተኛ ነው፤የአገር ውስጥ እግር ኳስ አፍቃሪዎችም የውጭ ተጫዋቾችን በመመልከት ይበልጥ የሚነቃቁበት አጋጣሚ ይፈጥራል። የውድድሩ ፋይዳ ይህ እስከሆነ ድረስ በመስተንግዶ ረገድ በቂ ዝግጅት ማድረግና አህጉራዊ ውድድሮች የማስተናገድ በቂ አቅም እንዳለ ማስመሰከር የግድ እንደሚል የሚገልፁት ረዳት ፐሮፌሰር ወንድሙ፤ በተለይ በሁሉም ክልልከተሞች ውስጥ ግንባታቸው ተጀምሮ ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቁትን ስቴዲየሞች፤ የማጠናቀቅ፣በተለይም ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ማስጠበቅ የግድ እንደሚል ነው ያመለከቱት፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ፤«አገሪቱ ውድድሩን ከማሰናዳት ባሻገር ለመድረኩ ጠንካራ ብሄራዊ ቡድን በማዘጋጀት ተወዳዳሪ ሆኖ መቅረብ እንዳለባት መዘንጋት የለበትም» የሚሉት ረዳት ፕሮፌሰሩ፤መወዳደር ብቻም ሳይሆን ውጤታማ ለመሆን ከወዲሁ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባ ይገልጻሉ። ይህ ካልሆነም ገና በመጀመሪያው ዙር መባረር እንደሚከተል፣ይህ ሲሆንም ስታዲየም ተገኝቶ ጨዋታዎችን የሚመለከት ተመልካችም እንደማይገኝ፣ ውጤቱም ግዙፍ ኪሳራ እንደሚያስከትል ማወቅ ይገባል ይላሉ፡፡ ከውድድሩ መስተንግዶ ባሻገር ጠንካራ ቡድን ይዞ ለመቅረብ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚያስፈልግ አፅዕኖት ተናግረዋል። የስፖርት ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ናስር ለገሰ ፤ ኢትዮጵያ የቻን ዋንጫን እኤአ በ2020 ለማስተናገድ ከካፍ ኃላፊነቱን ከተረከበች ዓመታት ማለፋቸውን ያስታውሳሉ። «በአሁኑ\nወቅትም ይህን የዝግጅት አደራ በስኬት ለመወጣት እቅድ ወጥቶ ወደ ስራ ተገብቷል፤ዝግጅቱን ለመገምገም ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የካፍ ልዑካን ቡድን በሰጠው ምክረ ሃሳብ መሰረት ክልሎችም የሀዋሳ፤ የባህር ዳር፤የመቀሌ ስታዲየሞችን የማዘጋጀት ተግባር እያከናወኑ ናቸው»ያሉት አቶ ናስር፤ኮሚሽኑም የስታዲየሞቹ ግንባታ ሂደት በተሻለ ፍጥነት ጥራቱን ጠብቆ ሙሉ በሙሉ እንዲጠናቀቅ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን ያብራራሉ። አገሪቱ አደራዋን በስኬት ለመወጣት እየተንቀ ሳቀሰች እንደሆነ ቢገለፅም፣ ውድድሩ እየተቃረበ በመጣበት በዚህ ወቅት የመስተንግዶ ዝግጅት ፍጥነት ሲፈተሽ መጓተት እንደሚስተዋል በግልፅ ይታያል ፤በዚህ ላይ ምን ይላሉ በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ አቶ ናስር ሲመልሱም፤መስተንግዶው በቂ ፍጥነት እንደሌለው አልሽሸጉም። «ቻንን የመሰለ ታላቅ አህጉራዊ ውድድር ለማስተናገድ አስቀድሞ መዘጋጀት የሚገባ ቢሆንም፤ ኢትዮጵያ እያደረገች ያለችው ዝግጅት ግን በሚፈለገው ልክ እየተጓዘ አይደለም»ያሉት አቶ ናስር፤ውድድሩ እየተቃረበ ሲመጣ በርካታ ተግባራት መልክ መልክ እንደሚይዙና እንደሚሳኩ እምነታቸው መሆኑን ነው ያብራሩት።አዲስ\nዘመን የካቲት 26/2011በታምራት\nተስፋዬ", "passage_id": "1ed4486d7aba06ee06d65553bb87d448" }, { "passage": "በ2020 የአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ (ቻን) አስተናጋጅ የሆነችው ኢትዮጵያ ባለፉት ቀናት በካፍ ከፍተኛ ባለሙያዎች የስታዲየምቿ ዝግጅት ተገምግሟል።ይህን ውድድር ያስተናግዳሉ ተብለው የተለዩትና ሙሉ ለሙሉ ተገንብተው መጠናቀቅ ያልቻሉት የሀዋሳ፣ መቐለ፣ ባህርዳር እና የአደይ አበባ ስታዲየሞችን ባሳለፍነው ዓመት ከካፍ በተላኩ ባለሙያዎች አማካኝነት በመዟዟር የተጎበኙ ሲሆን በዚህ ሳምንትም የመጨረሻው የግምገማ ምዕራፍ ተካሂዷል። የካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት የሆኑት ሊሆድጋር ቴንጋ እና ሞሰስ ማጎጎ፣ የካፍ የክለቦች ፍቃድ ሰጪ ኃላፊ አህመድ ሀራዝ እና ሁለት የሚዲያ ባለሙያዎች ሐሙስ ወደ አዲስ አበባ ከገቡ በኃላ ዓርብ በሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ጉብኝታቸውን በማድረግ ነበር የግምገማ ጅማሮ ያደረጉት።በመቀጠል ቅዳሜ ወደ መቐለ በማምራት የትግራይ ዓለም አቀፍ ስታዲየምን በመጎብኘት ግምገማ አድርገዋል። የመጫወቻ ሜዳውን እንዲሁም በስታዲየሙ ቅጥር ጊቢ የተሰራውን የመለማመጃ ሜዳ እና የመቐለ ዩኒቨርሲቲን ስታድየም የጎበኙ ሲሆን በተለይ የዓለም አቀፉን ስታድየም ውስጣዊ እና ውጫዊ አካል በመጎብኘት በሀዋሳ ስታዲየም የተገጠመው መብራት በመቐለ አለመከናወኑን እንደ ጉድለት ማንሳታቸው ታውቋል።ዕሁድ የሶስተኛ ጉብኝታቸው መዳረሻን ባህር ዳር በማድረግ ዓለም አቀፍ ስታድየም፣ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ (ፔዳ ጊቢ)፣ የአፄ ቴዎድሮስ ስታድየም ከመለማመጃ ሜዳው ጋር ተመልክተዋል። ትላንት ከሰዓት ደግሞ በግንባታ ላይ የሚገኘው የአደይ አበባ ስታዲየምን ከተመለከቱ በኋላ የሚጠናቀቅበትን ጊዜ አስመልክቶ ጥያቄ አቅርበዋል። ለልምምድ ያገለግላሉ የተባሉትን በወጣቶች አካዳሚ ያሉ ሁለት የመለማመጃ ስፍራን ጨምሮ አንጋፋውን የአዲስ አበባ ስታዲየም የተመለከቱ ሲሆን አንድ የመለማመጃ ሜዳ ግን በቶሎ መሰራት እንዳለበት ለፌዴሬሽኑ ማሳሰባቸው ተነግሯል፡፡ ያለፍትን አምስት ቀናት የቻን 2020 የዝግጅት ግምገማን በማጠናቀቅም ትላንት ምሽት የተመለሱ ሲሆን ልዑኩ በቀጣይ ሳምንት የግምገማውን ውጤት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን እና ለሀገሪቱ መንግስት እንደሚልክ ተሰምቷል።ረጅም የግንባታ ዓመታት የወሰዱት እና እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ያልተጠናቀቁ በርካታ ስታድየሞች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ የቻን ውድድርን ለማካሄድ ከአንድ ዓመት ያነሰ ጊዜ በቀረበት በዚህ ወቅት ከሚመለከታቸው አካላት ስለ መስተንግዶው ቅድመ ዝግጅት እና እስካሁን እየተሰሩ ስላሉ ስራዎች ይፋዊ መረጃ እየተሰጠ የማይገኝ መሆኑ አሳሳቢ ሆኗል። ከዚህ በተጨማሪም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ መሟላት ከሚገባቸው በርካታ ጉዳዮች አንዱ የሆነው የስታድየም ቅድመ ሁኔታዎች (ደረጃውን የጠበቀ የመጫወቻ ሳር፣ የተጠባባቂ ተጫዋቾች እና የቡድን አመራሮች መቀመጫ፣ ፓውዛ፣ በስታድየሙ የተለያዩ ክፍሎች የሚገጠሙ የኤሌክትሮኒክስ መሳርያዎች፣ በቂ የመልበሻ ክፍል፣ የሚዲያዎች እና የጋዜጣዊ መግለጫ ክፍል፣ በቂ መፀዳጃ ክፍሎች፣ በአንድ ከተማ እስከ አራት የልምምድ ሜዳ) እና የመሳሰሉትን በቀሪዎቹ ወራት የማሟላት ኃላፊነት ይጠበቅባታል።", "passage_id": "0c720095e89a2f856090dc8efdf112d3" }, { "passage": "እ.አ.አ በ2019 ለ5ኛ ጊዜ የሚካሄደው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ቻን) ዋንጫ በካሜሩን ይስተናገዳል፡፡ በየሁለት ዓመቱ በሚደረገው ውድድር ላይ ተሳታፊ ለመሆን አገራት ከወዲሁ የማጣሪያ ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ። የአፍሪካ እግር ኳስ ማህበር (ካፍ) ባወጣው መርሃ ግብር መሠረት በሚደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያና ሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ሁለቱ ቡድኖች ከሦስት ሳምንታት በፊት በመቐለ ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን፤ የመልሱን ጨዋታ ጥቅምት 8 ቀን 2012 ዓ.ም ኪጋሊ ላይ የሚያደርጉ ይሆናል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ በመቐለ ከተማ ትግራይ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ከሦስት ሳምንታት በፊት በሩዋንዳ 1ለ0 ሽንፈትን ማስተናገዳቸው ይታወቃል፡፡ ዋልያዎቹ የመቐለውን ሽንፈት ለማካካስ ለመልሱ ጨዋታ ከወዲሁ ዝግጅታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ። በኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ የሚመራው ቡድን ከመስከረም 26 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለ24 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ በአዳማ ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል። ኢንስትራክተር አብርሃም በቡድኑ ስብስብ አብዛኞቹ ተጫዋቾች ለኳታሩ የዓለም ዋንጫ ከሌሶቶ ጋር በነበራቸው የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ የተመረጡት መሆናቸው ለቡድኑ ቅንጅትም ጠቃሚ እንደሆነ ታምኖበታል። ብሔራዊ ቡድን ከአዳማው ዝግጅት በተጨማሪ ከዩጋንዳ ጋር በዛሬው ዕለት የአቋም መፈተሻ የወዳጅነት ጨዋታውን ያደርጋል። በባህር ዳር ስታዲየም የሚካሄደው ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የሥነ ልቦና ዝግጅት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተነግሯል። ኢንስተራከተር አብርሃም ከመቐለ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ በመልሱ ጨዋታ ሩዋንዳ ኪጋሊ ላይ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል ዝግጅት እንደሚያደርጉ ቃል መግባታቸው ይታወቃል፡፡ አሰልጣኙ ከሽንፈቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት በመልሱ ጨዋታ ውጤት ለመቀልበስ እንደሚሰሩ ነበር ያስተወቁት። «በሜዳችን በነበረን ጨዋታ ብዙም ብልጫ ሳይወሰድብን በጥቃቅን ስህተት ነው ግቡ የተቆጠረብን። ከዚህ ውጪ ግን አስፈሪ የሚባል ነገር አልገጠመንም። በመሆኑም በመልሱ ጨዋታ ከዚህ በተሻለ ተንቀሳቅሰን ውጤት ይዘን ለመምጣት የተቻለንን እናደርጋለን።›› ሲሉ ቡድናቸው በጨዋታ ድል ባይቀናውም በመልሱ ጨዋታ ውጤት ለመቀልበስ ዝግጅት እንደሚደረግ ነው ያመላከቱት። አሰልጣኙ የቡድን ስብስብ በመያዝ ከአዳማ ዝግጅት በኋላ በዛሬው ዕለት በባህር ዳር ስታዲየም ከዩጋንዳ ብሔራዊ ቡድን የሚያደርገውን የአቋም መለኪያ ከሳምንት በኋላ ለሚጠብቀው ፈተና የተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች እንደሆኑ ታውቋል። ዋልያዎቹ በመጪው እሁድ በሩዋንዳ የሚያደርጉት ጨዋታ የብሔራዊ ቡድኑን ወደ ቻን የሚያደርጉት ግስጋሴ ወሳኝ ምዕራፍ ይሆናል። ብሔራዊ ቡድኑ መቐለ ላይ 1 ለ0 ሽንፈት ማስተናገዱ፤ ዋልያዎቹ ኪጋሊ ላይ የሚደረገው ጨዋታን ከሁለትና ከዚያ በላይ በሆነ ውጤት ማሸነፍ እንዲጠበቅባቸው ግድ አድርጎታል። ዋልያዎቹ በመድረኩ ለመታየት ያላቸውን አነስተኛ እድል ለመጠቀም፤ በመቐለ የነበሩ ክፍተቶች አሻሽለው መቅረብ እንደሚኖርባቸው ከስፖርት አዋቂዎች በኩል እየተነገረ ይገኛል። ብሔራዊ ቡድኑ ላይ በተለይ ከሌሴቶ፣ ከጅቡቲ እንዲሁም ከሩዋንዳ ጋር በነበራቸው ጨዋታ ጥሩ የሚባል እንቅስቃሴ ቢያሳዩም ኳስን ከመረብ የማዋሃድ ውስንነቶች በተደጋጋሚ ተስተውሎባቸዋል። በሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የተሻሉ ነገሮች ቢታዩም ተጫዋቾቹ ያገኟቸው የጎል አጋጣሚዎች የመጠቀም ክህሎታቸው ደካማ መሆን ብሔራዊ ቡድኑን ዋጋ እያስከፈሉት እንደሚገኙ ለመታዘብ ተችሏል። በሩዋንዳ 1 ለ0 ሽንፈትን ባስተናገዱበት ወቅት የነበሩት ስህተቶች ቀጥለው መታየታቸው ቡድኑን ለትችት ዳርገውታል። ዋልያዎቹ በዛሬው እለት ከዩጋንዳ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ማድረጋቸው የተጠቀሱትንና መሰል ክፍተቶቻቸውን እንዲመለከቱ እድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል። ኢንስትራክተር አብርሃም ብሔራዊ ቡድኑ የመልሱን ጨዋታ በድል ለመወጣት ከአካላዊም በተጨማሪ ሥነ ልቦናዊ ዝግጅት የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበዋል። ብሔራዊ ቡድኑ ለጨዋታው ትኩረት በተሞላበት ሁኔታ ዝግጅት በማድረግ ውጤት ለመቀልበስ ወደ ኪጋሊ የሚያቀና ይሆናል። የሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን ለኪጋሊው የመልስ ጨዋታ በተመሳሳይ ዝግጅቱን እያደረገ ሲሆን፤ ቡድኑ የአሸናፊነት ሥነ ልቦናን በመላበስ ጨዋታውን በአሸናፊነት ለመፈጸም እየተሰናዳ መሆኑን ተሰምቷል። የሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን በመቐለ ማሸነፍን ተከትሎ፤ በመጪው እሁድ በሜዳው በሚኖረው ጨዋታ የበላይነት ወስዶ ወደ ቻን የሚያደርገውን ግስጋሴ እውን ሊያደርግ ይችላል እየተባለ ይገኛል። የሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን በመልሱ ጨዋታ ሁለቱ ነጥቦች ቡድኑ በሥነ ልቦና ተጠናክሮ እንዲገባና የአሸናፊነት መንፈስ የሚያላብሱት በመሆኑ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ለማሸነፍ ከፍተኛ ግምት ወስዷል። በኢንስትራክተር አብርሃም የሚመሩት ዋልያዎቹ አነስተኛ የአሸናፊነት ተሰጥቷቸው ወደ ሜዳ ይገባሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሩዋንዳ ጋር በቻን ዋንጫ በሁለት የተለያዩ ታሪካዊ አጋጣሚዎች ተገናኝተዋል። እ.አ.አ በ2014 በደቡብ አፍሪካ አዘጋጅነት ለሚካሄደው 3 ኛው የቻን ዋንጫ ማጣሪያ የመጀመሪያው አጋጣሚ ነው። ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመድረኩ ተሳታፊ ስትሆን፤ በማጣሪያው ሩዋንዳን በደርሶ መልስ አሸንፋ ነበር። ጨዋታው በኪጋሊ ከተማ የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያ ሩዋንዳን በመለያ ምት 5ለ6 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩዋንዳን በመጣል ነበር፡፡ የሁለቱ ሀገራት ሌላው ፍጥጫ እ.አ.አ በ2017 በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ውድድር በማጣሪያው ተገናኝተዋል። በዚህም ሩዋንዳ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን በድምር ውጤት 3 ለ 2 በመርታት ወደ ሞሮኮ ስታቀና፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከመድረኩ ውጪ የሆኑባቸው ሁለት የታሪክ አጋጣሚዎች እንደነበሩ ይታወሳል። የሁለቱ አገራት ሌላው ታሪካዊ ፍጥጫ በመጪው እሁድ ጥቅምት 8 ቀን 2012 ዓ.ም ኪጋሊ ላይ ትዕይንት ይሆናል። አዲስ ዘመን ጥቅምት 2/2012 ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "37523939761950a5e16572a3c1553b61" } ]
7e04ba08911309739e6193c571693f7b
d6202e31853222632ea578e0bf2aed5a
የቶኪዮ ኦሊምፒክ የጎዳና ላይ ውድድሮች ስፍራ ተቀየረ
በ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድሮች የሚካሄድባቸው ስፍራዎች መቀየር ላይ ሲነሳ የቆየው አወዛጋቢ ሃሳብ መቋጫ አግኝቷል፡፡ የኳታር ዓለም ቻምፒዮና የማራቶን ውድድር ላይ የታየውን ክስተት ተከትሎ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከዓለም አትሌቲክስ ጋር በመሆን ውድድሩ የሚካሄድበት ስፍራ እንዲቀየር ጥያቄ ማንሳታቸው የሚታወስ ነው፡፡ የቶኪዮ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴው በበኩሉ የውድድር ስፍራውን ከቶኪዮ ወደ ሌላ ስፍራ የማዘዋወር ዓላማ እንደሌለውና በሃሳቡም እንደማይስማማ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ትናንት በወጣው ዜና መሰረትም በውድድሮቹ ላይ የመርሃ ግብር ቅየራ መደረጉ ታውቋል፡፡ በዚህም መሰረት የማራቶን እና የእርምጃ ውድድሮቹ ከቶኪዮ በ800ኪሎ ሜትር ርቀት በሆካኢዶ ተራራማ አካባቢዎች በሚገኘውና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ባለው ሳፖሮ የተባለ ከተማ የሚካሄዱ ይሆናል፡፡ የውድድር ስፍራውን መቀየር ተከትሎ መርሃ ግብሮቹም ላይ ለውጥ የተደረገ ሲሆን፤ የሴቶች ማራቶን እና በሁለቱም ጾታ የእርምጃ ውድድሮች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይካሄዳሉ፤ የወንዶች ማራቶን ደግሞ እንደተለመደው የኦሊምፒኩ የመዝጊያ ውድድር ይሆናል፡፡ ሁለቱ ዓለም አቀፍ ተቋማት አትሌቶችን ከጉዳት ለመጠበቅ ሃሳቡን በቅድሚያ ያነሱት ሲሆን የውድድሩ አዘጋጆች ተቃውሟቸውን ሽረው ይሁንታቸውን ለመስጠት ምክንያት የሆነው የጃፓን ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲሁም የአትሌቶች ማህበር መሆኑን ስካይ ስፖርት አስነብቧል፡፡ ከውሳኔው ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን የሰጡት በዓለም ዓቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ የአትሌቶች ኮሚሽነር ክርስቲ ኮቬንተሪ፤ የአትሌቶች ጤና ከሁሉ አስቀድሞ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አያይዘውም ‹‹የማራቶን እና እርምጃ ውድድሮችን ከቶኪዮ ወደ ሳፖሮ መውሰዳችንም በአትሌቶች ጉዳይ ምን ዓይነት አቋም እንዳለን የሚያሳይ ነው›› ብለዋል፡፡ ወራት ብቻ የቀሩት ኦሊምፒኩ በሚካሄድበት ወቅት በጃፓኖች ዘንድ በጋ ነው፤ በጊዜው የቶኪዮ የሙቀት መጠን ደግሞ እስከ 30ዲግሪ ሴሊሽየስ በማሻቀብ ከፍተኛ ወበቅ የሚያስከትል ይሆናል፡፡ ይህ ደግሞ ረጃጅም ርቀት ለሚሸፍኑት የውድድር ዓይነቶች የማይስማማ በመሆኑ በኳታር ያጋጠመው እንዳይደገም ያሰጋል፡፡ የውድድሩ አዘጋጆችም ሙቀቱን ለመቋቋም፤ መጠለያዎችን በማበራከት፤ የውሃ ማቀዝቀዣና ከፍተኛ የውሃ አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ እንዲሁም አትሌቶች ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ማሰባቸውን ነበር ያሳወቁት፡፡ሆኖም በዓለም አቀፎቹ ተቋማት በተደረገው ግፊት የውድድር ስፍራው እንዲለወጥ ተደርጓል፡፡ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስራ አስኪያጅ ቶሺሮ ሙቶ ‹‹በሳፖሮ የሚገኘው የኦዶሪ ፓርክ ለእነዚህ ውድድሮች የተመቸ ስፍራ ነው፡፡ በመሆኑም ውሳኔውን ተከትለን በፍጥነት ቦታውን በማዘጋጀት ላይ እንገኛለን፡፡ ኦሊምፒኩ ስምንት ወራት ብቻ ቢቀሩትም በትብብር ዝግጁ የምናደርገው ይሆናል›› ሲሉም ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡አዲስ ዘመን አርብ ህዳር 26/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23653
[ { "passage": "የዓለም ትልቁ ስፖርታዊ ውድድር ኦሊምፒክ ከመካሄዱ አንድ ዓመት አስቀድሞ ይካሄዳል። በተለያዩ ክፍለ አህጉራት የሚካሄደው ይህ ውድድር እንደ ኦሊምፒክ የሚታይ ሲሆን፤ የአህጉሩን አገራት በተለያዩ ስፖርቶች ያወዳድራል። በአፍሪካም እ.ኤ.አ 1965 ለመጀመሪያ ጊዜ ሲካሄድ፤ በየአራት ዓመቱ እየተዘጋጀ አሁን 12ኛ ጊዜ ላይ ደርሷል። ውድድሩ እ.ኤ.አ እስከ 2012 የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በሚል ሲጠራ ቢቆይም፤ አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው ጉባኤ የአፍሪካ ጨዋታዎች በሚል እንዲሻሻል ተደርጓል። በአፍሪካ ሕብረት፣ በአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበራት እንዲሁም በአፍሪካ ስፖርት ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አስተባባሪነት ይካሄዳል። የአፍሪካ ሕብረት የውድድሩ ባለቤት ሲሆን፤ የኦሊምፒክ ኮሚቴዎቹ ማህበር ቴክኒካዊ ጉዳዮችን በመምራት እንዲሁም ኮንፌዴሬሽኑ ከገንዘብ እና ከስፖንሰሮች ጋር የተያያዘውን ጉዳይ በማስተባበር ተሳትፏቸውን ያደርጋሉ። በዓለም አቀፉ\nየኦሊምፒክ ኮሚቴ በበላይነት የሚመራው አህጉር አቀፉ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ በኮንጎ ብራዛቪል ነበር የተካሄደው። በዚህ ውድድር ላይ ተሳታፊ የሚሆኑት የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አባል አገራት ሲሆኑ፤ በአፍሪካ አቀፉ ውድድር ላይም 53ቱም አባል አገራት ተካፋይ ነበሩ። የኦሊምፒክን ጽንሰ ሐሳብ ተከትሎ የሚካሄደው ውድድሩ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነትን ይቃወማል። ከዚህ ቀደም በደቡብ አፍሪካ በነበረው የአፖርታይድ ሥርዓት እንዲሁም በሞሮኮ ተከስቶ በነበረው ፖለቲካዊ ቀውስ ምክንያት አገራቱን ከተሳታፊነት አግልሎም ነበር። የዘንድሮው ውድድር በሞሮኮዋ ራባት\nየሚካሄድ ሲሆን፤ 53አገራት በ23 የስፖርት ዓይነቶች ብሔራዊ ቡድኖቻቸውን ያሳትፋሉ። በቀጣዩ ወር\nየሚጀመረው ውድድሩ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱን በንጉሥ ሞሐመድ 6ኛ ስታዲየም እንደሚደረግ ይጠበቃል። አገሪቷ በአጠቃላይ ለውድድር እንዲሁም ለልምምድ የሚሆኑ 13 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችንም አዘጋጅታ ተሳታፊዎቿን በመጠባበቅ ላይ\nትገኛለች። በዚህ ውድድር ተሳትፎ በርካታ ሜዳሊያዎችን በማስቆጠር በሰንጠረዡ አናት የተቀመጠችው ግብጽ 1ሺ362 ሜዳሊያዎችን ሰብስባለች። ሁለተኛዋ አገር\nናይጄሪያ በበኩሏ 1ሺ199 ሜዳሊያዎች አሏት። ደቡብ\nአፍሪካ ደግሞ በ967 ሜዳሊያዎች ሦስተኛ ደረጃ\nላይ ትገኛለች። ስምንተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ኢትዮጵያ 122 ሜዳሊያዎች ሲኖሯት፤ ከእነዚህ መካከል 39ኙ የወርቅ፣ 39ኙ\nየብር እንዲሁም 52 ቱ የነሐስ ሜዳሊያዎች ናቸው። ከአራት ዓመታት በፊት\nበኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ ኢትዮጵያ ኬንያን በመከተል ስምንተኛ ሆና ያጠናቀቀች ሲሆን፤ 6 የወርቅ፣ 5 የብር እና 6 የነሐስ በጥቅሉ 17 ሜዳሊያዎችን ነበር ያስመዘገበችው። ኢትዮጵያ በዘንድሮው ውድድር በ13 የስፖርት ዓይነቶች የምትሳተፍ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nአስታውቋል። የተወሰኑ ስፖርቶች ዝግጅታቸውን ሲጀምሩ ሌሎች ደግሞ ተሳታፊ ስፖርተኞቻቸውን ለመምረጥ ሻምፒዮናዎችን እያካሄዱ ይገኛሉ። የስፖርት ዓይነቶቹም፤ አትሌቲክስ፣ ብስክሌት፣ ቦክስ፣ ካራቴ፣ ወርልድ ቴኳንዶ፣ ቼስ፣ ክብደት ማንሳት፣ የውሃ ስፖርቶች፣ ጂምናስቲክ፣ ቅርጫት ኳስ፣ ባድሜንተን፣ ጠረጴዛ ቴኒስ እና ሜዳ ቴኒስ ናቸው። ቀድመው ወደ ዝግጅት ከገቡት ስፖርቶች መካከል አንዱ ኢትዮጵያ የምትታወቅበትና ውጤታማ የሆነችበት የአትሌቲክስ ስፖርት አንዱ ነው። በዚህ ውድድር የሚሳተፉ አትሌቶች በግንቦት ወር የተመረጡ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ሆቴል ተቀምጠው ዝግጅት በማድረግ ላይም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር ከ100-10ሺ\nሜትር ባሉት የሩጫ እና የሜዳ ተግባራት ስትካፈል፤ በጥቅሉ105 አትሌቶች ተመርጠዋል። አትሌቶቹ ሊመረጡ የቻሉትም ከወራት በፊት በተካሄደው 48ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታወቋል። ሌላኛው ዝግጅቱን አስቀድሞ የጀመረው ስፖርት ቦክስ ሲሆን፤ በ7 ወንድ\nእና 2 ሴት ቦክሰኞች ብሔራዊ ቡድኑ እንደሚወከል ከኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ይጠቁማል። በወንዶች ምድብ የተመረጡት ቦክሰኞች፤ በ49፣56፣ 60፣ 64፣ 69፣ 75 እና 81 ኪሎ ግራሞች በውድድሩ ላይ ይሳተፋሉ። በሴቶች በኩል ደግሞ በ48 እና\n51 ኪሎ ግራሞች ተካፋይ ይሆናሉ። በየዓመቱ በአራት ዙሮች ከሚካሄደው የኢትዮጵያ ክለቦች ሻምፒዮና የተመረጡት ቦክሰኞቹ በሦስቱ ዙር የተሻለ ብቃት በማሳየታቸው የተመረጡ መሆናቸውም ታውቋል። ሌላኛው ተሳትፎ የሚደረግበት ስፖርት ብስክሌት፤ በመቀሌ ከሰኔ 19- 22 በተካሄደው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ተመርጠዋል። እስከ ሐምሌ አንድ ቡድኑን የሚቀላቀሉት ብስክሌተኞች ታውቀው ወደ ዝግጅት የሚገቡ ሲሆን፤ በሁለቱም ፆታ በሚካሄዱት ሁሉም የውድድር ዓይነቶች ለመሳተፍ ማቀዱን ፌዴሬሽኑ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ገልጿል። በክብደት ማንሳት ስፖርትም በተመሳሳይ ተካፋይ የሆኑ ስፖርተኞች የሚመረጡበት አገር አቀፍ ሻምፒዮና ተካሂዷል። በወንዶች ከ55-102 ኪሎ\nግራም በሴቶች ደግሞ ከ45-71 ኪሎ\nግራም በተካሄደው በዚህ ውድድር በሁለቱም ፆታዎች አገርን የሚወክሉ ስፖርተኞች ይመረጡበታል። አዲስ ዘመን ሀምሌ\n15/2011 ", "passage_id": "ef46719f090fdff1a8afb7fbe0c9c9dd" }, { "passage": "የዓለምን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ወደተለየ አቅጣጫ ያዞረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በስፖርቱ ዓለም ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተዘርዝሮ የሚልቅ አይደለም።አንዳች ውድድር በዓለም ላይ እንዳይኖር ከማስገደድ ባለፈ የስፖርቱን ዓለም ሽባ አድርጎታል።ብዙ ታቅዶባቸው፣ ብዙም ተለፍቶባቸው ለዓመታት በዝግጅት ላይ የነበሩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በትልቅ ኪሳራ የሚካሄዱበት ጊዜ እንዲራዘም ግድ ብሏል። \nጃፓን ካለፉት ሰባት ዓመታት በላይ ከፍተኛ ዝግጅት ስታደርግበት የቆየችው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በትልቅ ኪሳራ ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረ ታላቅ የስፖርት መድረክ ነው።ይህን ታላቅ የስፖርት መድረክ ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ እየተናነቀውም ቢሆን ለ2021 ለማራዘም ተገዷል።ኦሊምፒኩን ጨምሮ በርካቶቹ ዓለም አቀፍ የስፖርት ውድድሮችና ጉባዔዎች ወደ ቀጣይ ዓመት የተሸጋገሩት የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በቁጥጥር ስር ይውላል በሚል ተስፋ ነው።ይሁን እንጂ በዓለም ላይ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ከተስፋ በስተቀር የቫይረሱ ስርጭት በጊዜ የሚገታ ወይም ፈውስና ክትባት በዚህ ጊዜ እውን ይሆናል የሚያስብል እንዳልሆነ መታዘብ ይቻላል።ይህንን ከግምት ያስገቡት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ኦሊምፒኩ የቫይረሱን ስጋት ለማምለጥ በአስራ ስድስት ወራት ቢራዘምም ከቫይረሱ ተፅዕኖ ሊያመልጥ እንደማይችል ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ማመልከታቸውን አሶሼትድ ፕሬስ አስነብቦታል። \nየዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩ ወደ 2021 እንዲዘዋወር ውሳኔ ላይ ከደረሰ ወዲህ በቫይረሱ ስጋት በአስተናጋጇ ጃፓን ቶኪዮን ጨምሮ በሰባት ከተሞች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል።ከቀናት በፊት የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱትም በኮሮና ቫይረስ በጃፓን ከስድስት ሺ በላይ ሕዝቦች ሲጠቁ ከመቶ በላይ የሚሆኑት ሕይወታቸውን አጥተዋል።ኦሊምፒኩ እስከሚካሄድ ገና አስራ ስድስት ወራት የቀሩት ቢሆንም የቫይረሱን ስርጭት በነዚህ ጊዜያት በቁጥጥር ስር ማዋል ካልተቻለ ኦሊምፒኩ አሁንም ከስጋት ውጪ ሊሆን እንደማይችል ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።‹‹በዚህ ወቅት ማንም በእርግጠኝነት ቫይረሱን በቁጥጥር ስር አውላለሁ የሚል እምነት የለውም፣ ስለዚህ የተራዘመው ኦሊምፒክ ከቫይረሱ ስጋት ነፃ ይሆናል ብለን ለመናገር ይቸግረናል›› በማለትም ሃሳባቸውን አጠናክረዋል። \nበቫይረሱ ስጋት ኦሊምፒኩን ከአንድ ዓመት በላይ ለማራዘም እንደተወሰነ ያስታወሱት ስራ አስፈፃሚው፣ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዚህ ወቅት ለተራዘመው ኦሊምፒክ ጠንክሮ ከመዘጋጀት ውጪ ሌላ ነገር ሊያደርግ እንደማይችል አስረድተዋል።ይሁን እንጂ የሰው ልጅ እስከዚያው ቫይረሱን በቁጥጥር ስር ያውላል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልፀዋል።የተራዘመው ኦሊምፒክ ዘንድሮ ሊካሄድ በታቀደበት ተመሳሳይ ወቅት እንዲካሄድ ከመወሰኑ ውጪ በየትኛው ቀን እንደሚካሄድ ቁርጥ ያለ ቀን አልተቀመጠለትም።ይህንንም ለመወሰን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የተለየ አማራጭ እስካሁን እንዳልተመለከተ አስረድተዋል።ከዚህ ይልቅ ኦሊምፒኩን ቀጣይ ዓመት ላይ በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የተቻለውን ሁሉ ጥረት ማድረግ የሚቻልበትን አማራጭ ታሳቢ በማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። \nየቶኪዮ ኦሊምፒክ ወደ ቀጣዩ ዓመት በመራዘሙ ብቻ በጃፓንም ይሁን በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እንደሚያስከትል ቀደም ሲልም ሲነገር ነበር።ይሁን እንጂ ይህ ኪሳራ ምን ያህል እንደሚሆን አሁን ላይ ማስቀመጥ ከባድ እንደሚሆን ስራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል።ነገር ግን ኪሳራው ከባድ እንደሚሆን አስቀምጠዋል። \nየኦሊምፒክ ውድድሩ ከመራዘሙ አስቀድሞ የወጡ ጥናቶች እንዳመለከቱት ኦሊምፒኩ ከተሰረዘ ወይም ከተራዘመ የጃፓን ጠቅላላ የአገር ውስጥ ገቢዋ 1ነጥብ 4 በመቶ ሊያሽቆለቁል እንደሚችል ተጠቁሟል።ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ የጃፓን መንግስትን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ እንደሚገቡ ቀደም ሲል ተዘግቧል።የጃፓኑ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም ገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ ኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል ተናግሯል።ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለዚህ ኪሳራ ስጋት ሰላሳ ሦስቱንም ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን የገባ ቢሆንም በቂ እንደማይሆን ታምኖበታል።ፕሬዚዳንቱ ቶማስ ባኽም ኦሊምፒኩ መራዘሙን በገለፁበት ወቅት ከባድ ኪሳራ እንደሚኖር በማመን ሁሉም ባለድርሻ አካላት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል፡፡አዲስ ዘመን ሚያዝያ 8/2012 ", "passage_id": "7d2188a7787361b54ce55de5bef8b537" }, { "passage": "የዓለምን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ወደተለየ አቅጣጫ ያዞረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በስፖርቱ ዓለም ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተዘርዝሮ የሚልቅ አይደለም። አንዳች ውድድር በዓለም ላይ እንዳይኖር ከማስገደድ ባለፈ የስፖርቱን ዓለም ሽባ አድርጎታል። ብዙ ታቅዶባቸው፣ብዙም ተለፍቶባቸው ለዓመታት በዝግጅት ላይ የነበሩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በትልቅ ኪሳራ የሚካሄዱበት ጊዜ እንዲራዘም ግድ ብላል። \nየኮሮና ቫይረስ ስርጭት በዓለም ዙሪያ ከተንሰራፋ ወዲህ በግለሰብ ደረጃ ካልሆነ በስተቀር የትኛውም የስፖርት እንቅስቃሴ ተገድቦ እንደቆየ ይታወቃል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ይመለሳሉ የሚል ተስፋ የለም። ይሁን እንጂ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሐግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር እንደሚመለሱ ተስፋ መስጠታቸው አልቀረም። የዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን ለግሰዋል። \nበዓለማችን ብሎም በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ስርጭትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የስፖርት ቤተሰቡ መደበኛ እንቅስቃሴውን ገቶ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ ከጀመረ ሰነባብቷ። የስፖርት ቤተሰቡ ወረርሽኙን ለመከላከል ግንዛቤ ከመፍጠር እስከ ደም ልገሳ፤ ከቁሳቁስ እስከ ገንዘብ ድጋፍ በማድረግ አጋርነቱን አሳይቷል ፤ በማሳየት ላይም ይገኛል። \nወረርሽኙ በዓለም ላይ ከተከሰተና ከተስፋፋ ወዲህ የስፖርቱን ዘርፍ ክፉኛ የጎዳው ሲሆን የአገራችንን ጨምሮ በዓለም ላይ በርካታ ታላላቅ ውድድሮች እንዲቆሙ አስገድዷቸዋል። በተለይም ወረርሽኙን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በተወሰዱ እርምጃዎች ስልጠናዎች፣ ውድድሮች ቁመዋል ፤ ስፖርተኛው እና የስፖርት ቤተሰቡ ከፍተኛ የሆነ የስነ ልቦና እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አጋጥሟቸዋል ። \nበርካታ የስፖርት ክለቦች የመፍረስ አዳጋ ተደቅኖባ ቸዋል፤ አንዳንዶቹም ለስፖርተኞች ወርሃዊ ደመወዝ እስከ መከልከል ደርሰዋል። በመሆኑም የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በወረርሽኙ ወቅት እና ከወረርሽኙ በኋላ ስፖርቱ እንዴት ወደ ነበረበት መመለስ ያስችላል የሚለውን የሚያጠና እና ለመንግሥት የሚያቀርብ ጠንካራ ኮሚቴ መቋቋሙን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጅሎ መናገራቸውን የተቋሙ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ ላይ ተዘግቧል። \nየተቋቋመው ኮሚቴ አብይ እና ቴክኒካል ኮሚቴ ያለው ሲሆን አብይ ኮሚቴው በባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ጣሰው የሚመራ ይሆና። ቴክኒካል ኮሚቴው ደግሞ በአቶ ዱቤ ጅሎ እንደሚመራ ታውቋል። \nኮሚቴው አጠቃላይ የኮሮና ወረርሽኝ በአገራችን ስፖርት ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና እና መፍትሔዎችን በማጥናት ሰነዱን ለመንግሥት የሚያቀርብ ይሆናል። በጥናቱም የሌሎች አገራት ተሞክሮ ምን እንደሚመስል ተካቶ እንደሚቀርብ አቶ ዱቤ አብራርተዋል። \nጥናቱን መሠረት በማድረግ መንግሥት ስፖርቱ ለአገራችን ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ ግምት ውስጥ በማስገባት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምክትል ኮሚሽነሩ ገልፀዋል ።አዲስ ዘመን ግንቦት 27/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "24c212eb0cbc2bfc4fa9a396312bd847" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የዘንድሮ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ውድድር ለሌላ ጊዜ እንዲዛወር በአስተናጋጇ ሀገር ጃፓንና በዓለም ኦሊምፒክ ኮሚቴ ላይ ጫናው በርትቷል።በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ካናዳ በውድድሩ እንደማትሳተፍ ማስታወቋን ተከትሎ በርካቶች ውድድሩ ሌላ ጊዜ እንዲዛወር እየጠየቁ ነው።ካናዳ ከአትሌቶቿ ጤና የሚበልጥ ነገር እንደሌላ በማሳወቅ ነው ውድድሩ በተያዘለት ጊዜ የሚካሄድ ከሆነ እንደማትሳተፍ ያስታወቀችው።የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ በዛሬው እለት ውድድሩ ከዚህ ቀደም ሲካሄድ በነበረው ልክ መካሄድ የማይችል ከሆነ ለሌላ ጊዜ ይዛወራል ብለዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውድድርን ሙሉ በሙሉ መሰረዝ አማራጭ እንዳልሆነ እና የሚሻለው ለሌላ ጊዜ ማዛወር መሆኑንም ነው ያመለከቱት።በጉዳዩ ላይ አስቸኳይ ስብሰባውን ያደረገው የዓለም ኦሊምፒክ ኮሚቴ በፈረንጆቹ የፊታችን ሀምሌ 24 እንዲጀመር ቀን ተቆርጦለት የነበረው ውድድር ምናልባትም ለሌላ ጊዜ ሊዛወር የሚችልበትን ሁኔታ እየተመለከተ መሆኑንም አስታውቋል።ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!\nhttps://t.me/fanatelevision", "passage_id": "c408a5e126edfc2e09afbc285c07c9a4" }, { "passage": "የዓለም ታላቁ ስፖርታዊ ውድድር ኦሊም ፒክ፤ በየወቅቱ አዳዲስ የውድድር ዓይነቶችን በማካተት ይታወቃል። ፓሪስ\nበታሪኳ ለሶስተኛ ጊዜ እአአ በ2024 በምታስተናግደው ኦሊምፒክ ላይም አዳዲስ ውድድሮች የሚጨመሩ መሆኑ ታውቋል። የመጀመሪያው በማራቶን\nስፖርት ላይ መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውንም ሰው ማካተት ሲሆን፤ «ብሬክ» በመባል የሚታወቀው ዳንስ፣ በ«ስኬት ቦርድ» መንሸራተት፣\nበውሃ ላይ መንሳፈፍ እንዲሁም ተራራ መውጣት የኦሊምፒኩ የውድድር ዓይነቶች ናቸው።ከአትሌቲክስ ስፖርቶች ረጅሙን ርቀት የሚሸፍን ውድድር እንደመሆኑ ከፍተኛ ጽናትና ጥንካሬን ይጠይቃል፤ ማራቶን።\n42ኪሎ ሜትር መሸፈኑ ከባድ ቢያደርገውም በተለያዩ የዓለም ከተሞች በየሳምንቱ የሚካሄድ የውድድር ዓይነት በመሆኑ ብዙዎች ይሳተፉበታል።\nበተለይ በዚህ ርቀት እንደ ኦሊምፒክ ባሉ የውድድር መድረኮች ተሳትፎ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ከፍተኛ ክብርን ያስገኛል። በዚህም\nምክንያት በኦሊምፒክ የርቀቱ ተካፋይ የሚሆኑት፤ ታዋቂና ልምድ ያላቸው አትሌቶች ናቸው። በፓሪስ ኦሊምፒክ ላይ ግን የትኛውም መሮጥ የሚፈልግ ሰው ተካፋይ መሆን እንደሚችል የዓለም ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nአስታውቋል። ይህንን ዜና ተከትሎም የኦሊምፒኩን አስተባባሪ ኮሚቴ በፕሬዚዳንነት የሚመሩት ቶኒ ኢስታንጉዌት «ውድድሩን ልዩ ለማድረግ\nአንድ እርምጃ ተራምደናል። በርካቶችን የሚያሳትፉ የተለያዩ ውድድሮችም እንዲካተቱ አድርገናል። ተሳ ታፊዎች በየትኛውም ደረጃ ላይ\nቢገኙም በኦሊምፒኩ የተለየ ልምድ እንዲኖራቸው ማድረግ እንፈልጋለን» ሲሉ ገልጸዋል።በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ እአአ ከ1970 እንደተጀመረ የሚነገረው «ብሬክ» የተባለው የዳንስ ዓይነት፤\nባሳለፍነው ዓመት በቦነስ አይረስ በተካሄደው የወጣቶች ኦሊምፒክ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ አንድ የውድድር ዓይነት ተካሂዶ ነበር።\nይህንን ተከትሎም በዋናው የኦሊምፒክ ውድድር ላይም ለማካተት መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ ይጠቁማሉ።  ሊቀመንበሩ አክለውም\nከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲሁም የስፖርት ማህበራት ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኙና ልምዱ በሌሎች ስፖርቶችም እንዲንጸባረቅ\nእንደሚሹም ገልጸ ዋል።አዲስ ዘመን የካቲት\n18/2011ብርሃን ፈይሳ __\n  ", "passage_id": "f353ba31d75c252e4f49b91071931a2d" } ]
7906ba8d719a16388bb66f7bcb1e7ace
54a31e997b69cf8e8eb5159a05b79e7a
አፍሪካን ያገለለው የዓለም አትሌቲክስ ሌጋሲ
 የኦሊምፒክ የ1500 ሜትር ቻምፒዮኑ እንግሊዛዊ አትሌት ሴባስቲያን ሎርድ ኮ የዓለም አቀፉን አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በፕሬዚዳንትነት ለመምራት ከአራት ዓመት በፊት የተመረጡት አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው የማህበሩ ጉባዔ ላይ ነበር። ኮ ከአራት ዓመት በኋላም ባለፈው መስከረም በዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ዋዜማ ላይ ማህበሩን ለቀጣይ አራት ዓመታት ለመምራት ይሁንታ አግኝተዋል። ዓለም አቀፍ ማህበሩ ስሙን ‹‹የዓለም አትሌቲክስ›› በሚል በቅርቡ ከመቀየሩ አስቀድሞ በቀድሞው የመካከለኛ ርቀት ኮከብ አትሌት ኮ ቆራጥ አመራር ሰጪነት በርካታ ነገሮችን እንደቀየረ ይታመናል። በተለይም የቀድሞ የማህበሩ ፕሬዚዳንት ሴኔጋላዊው ላሚን ዲያክ የአስራ አንድ ዓመት የስልጣን ዘመን በአትሌቲክሱ ዓለም የተበላሹ የአመራር ክፍተቶችን በመድፈን ረገድ ኮ የተሳካላቸው መሆኑን ብዙዎች ይመሰክሩላቸዋል። እኤአ ከ1999 እስከ 2015 ማህበሩን የመሩት ዲያክ መንበረ ስልጣናቸውን ባስረከቡ ማግስት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ዛሬ ላይ በሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ፓሪስ ውስጥ በቁም እስር ላይ ይገኛሉ። የሃምሳ አራት ዓመቱ ልጃቸው ፓፓ ማሳታም ዓለም አቀፍ ማህበሩን ተገን አድርጎ ህገ ወጥ ገንዘብ ህጋዊ በማድረግና ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም አብረው ወህኒ ወርደዋል። የክስ ሂደታቸውም በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማግስት መታየት ይጀምራል። በብዙ ዝቅጠት ውስጥ የነበረውን ማህበር ለመረከብ ኮ ከምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት አንስተው ያልገቡት ቃል የለም። አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ ማሸነፍ የቻሉት ኮ በአመራር ዘመናቸው ትኩረታቸውን በአትሌቶች፣ በውድድሮች፣ በልማት፣ ግልፅነትና ተጠያቂነት ባለበት የአመራር ጉዳዮች ላይ ማድረጋቸው የብዙዎችን ድምፅ እንዲገዙ አስችሏቸዋል። ባለፉት አራት ዓመታትም የዓለምን አትሌቲክስ ቀዳዳዎች እየፈለጉ በመድፈንና በስፖርቱ ስር ነቀል ለውጦችን በመተግበር ተመስግነዋል። የዓለም የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ሽልማት ባለፈው ሳምንት በሞናኮ ሲካሄድም የዓለም አትሌቲክስ የፅህፈት ቤት ሃላፊውና የኮ ቀኝ እጅ የሆኑት ብሪቶን ጆን ሪድገን ለመገናኛ ብዙሃን‹‹ ቀጣዩ ስራችን እድገት ነው›› ሲሉ ተደምጠዋል። ሪድገን በንግግራቸው ጥራት ያላቸው ውድድሮችን በየትኛውም ደረጃ መፍጠር ዋና አጀንዳቸው መሆኑንም አብራርተዋል። ለተመልካቾች፣ ለስፖንሰሮችና ለንግድ አጋሮች ከዓለም ቻምፒዮና ባሻገር በሌሎች ውድድሮች ምቾትን መፍጠርም የዓለም አትሌቲክስ በቀጣይ ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። ኮ እንዲሁም ካቢኔያቸው የዓለምን አትሌቲክስ በገቢ ከማሳደግና የውድድር ጥራትን ከመፍጠር አኳያ የጀመሩት መንገድ የሚጠላ ባይሆንም አካሄዱ ላይ ጥያቄ ያላቸው ወገኖች አልጠፉም። በተለይም አፍሪካውያን። ከ2020 ጀምሮ በዳይመንድ ሊግ ውድድሮች ላይ የተደረገው ለውጥ የጥያቄው መሰረት ሲሆን ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን ከዚህ ለውጥ በተቃራኒ የቆሙ የአትሌቲክስ አገራት ናቸው። አምስትና ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል ከዳይመንድ ሊጉ መቀነሳቸውን ተከትሎ የርቀቱ ፈርጥ የሆኑት ሁለቱ ጎረቤታሞች ቀደም ሲልም ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ሪድገን ለምስራቅ አፍሪካውያኑ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ ግን የተቀነሱት ርቀቶች ጥናት ተደርጎባቸው ከቴሌቪዥን ስርጭት ጋር እንዲስማሙና ለዓለም አትሌቲክስ የገቢ ምንጭ እንዲሆኑ ታስቦበት ውሳኔ ላይ እንደተደረሰ አብራርተዋል። ‹‹ዳይመንድ ሊግ ስፖንሰር የለውም፣ ውድድሩን የሚመለከቱ የስፖርቱ አፍቃሪዎች ቁጥርም እያሽቆለቆለ ነው፣ ዳይመንድ ሊግ ጥሩ ውድድር ነው፣ ስፖንሰሮችና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች የተሻለ እንዲሆን ይሻሉ›› በማለት ሪድገን ቃል በቃል ተናግረዋል። እንደ ሪድገን ገለፃ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች ይበልጥ ሳቢና ለቴሌቪዥን ስርጭት አመቺ እንዲሆኑ ቀደም ሲል በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት 120 ደቂቃዎች ያስፈልጉት ነበር። አሁን ግን በዘጠና ደቂቃዎች ውስጥ በሚተላለፍ ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት እንዲከናወኑ ለማድረግ ነው በተለያዩ አምስት አገራት ጥናት ተደርጎ ረጅም ርቀቶችን መቀነስ ያስፈለገው። በዚህ ጥናት ውስጥ ግን የዳይመንድ ሊጉ ድምቀቶች፣ የአትሌቲክሱ ዓለም ውበት የሆኑት ምስራቅ አፍሪካውያን አልተካተቱም። በውሳኔው ላይም ድምፃቸው አልተሰማም። ሪድገን ለዚህ ምላሽ ሲሰጡ‹‹ በቀጣዩ ዓመት ሙሉ መልሶ ምልከታ እናደርጋለን›› ከማለት ውጭ የተነፈሱት ነገር የለም። የዓለም አትሌቲክስ በዳይመንድ ሊግ ላይ ሃያ አምስት በመቶ ድርሻ አለው። በቅርቡም ከቻይና ግዙፍ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር የዳይመንድ ሊግ ውድድሮችን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ለማስተላለፍ ለአስር ዓመት የሚዘልቅ ስምምነት ማድረጉ ይታወቃል። ስለዚህ የዓለም አትሌቲክስ ዳይመንድ ሊጉ ላይ ለውጥ ለማድረግ በቻይና ተፅዕኖ ውስጥ ወድቋል ብለው የሚያምኑ የስፖርት ቤተሰቦች ጥቂት አይደሉም። ለዚህ ሌላ ማሳያው በዳይመንድ ሊጉ ለውጥ ለማድረግ ጥናት ሲካሄድ በአትሌቲክሱ ዓለም ትልቅ ድርሻ ያላቸው ምስራቅ አፍሪካውያን አገራት እያሉ ቻይና ተመራጭ መሆኗ ነው። ለዚህ ውሳኔ ይረዳቸው ዘንድ ኮ የዓለም አትሌቲክስ ትልቅ የስራ ሃላፊነቶች በራሳቸው አገር እንግሊዝ ዜጎች ቀደም ብለው እንዲያዙ ማድረጋቸው ማሳያ ተደርጎ ይቀርባል። ከኮ በተጨማሪ የዓለም አትሌቲክስ የፅሕፈት ቤት ሃላፊው እንዲሁም የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዋናው ሰው ጃኪ ብሮክ ዶይል እንግሊዛዊ መሆናቸውን እዚህ ላይ ልብ ይለዋል። በእርግጥ በዓለም አትሌቲክስ ውስጥ ይህ ነገር ብርቅ አይደለም። ከዚህ ቀደም ማህበሩን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩት የነበሩት ላሚን ዲያክ ከልጃቸው ጀምሮ ሌጋሲያቸውን የሚያስቀጥሉላቸው እንደ ፕሪሞ ኔቢሎ አይነት ጣልያናውያንን በማህበሩ ቁልፍ ቦታዎች አስቀምጠው ነበር። የዓለም አትሌቲክስ በቅርቡ ይፋ ያደረገው ‹‹ኮንቲኔንታል ቱር›› የተባለው ሁለተኛ ትልቅ ውድድር በተለያዩ አስር የዓለማችን ከተሞች እንዲካሄድ ውሳኔ ላይ ሲደረስ አብዛኞቹ የውድድሩ መዳረሻ ከተሞች በአውሮፓ የሚገኙ መሆናቸው ሌላ ጥያቄ የሚጭር ጉዳይ ነው። ከነዚህ ውድድሮች መካከል ዘጠኙ በየትኛው ከተማ እንደሚካሄዱ ተወስኗል። ቶኪዮ፣ ናንጂንግ፣ ኦስትራቫ፣ ሄንግሎ፣ ቱርኩ፣ ኪንግስተን፣ ዤክስፈርቫር፣ ሲሌሲያና ዛግሬብ ውድድሩ የሚካሄድባቸው ከተሞች ናቸው። የኬንያ የስፖርት ካቢኔ ፀሐፊ አሚና ሞሐመድ እንዲሁም የኬንያ አትሌቲክስ ዋና ፀሐፊው ኪሪሚ ካቤሪያ ይህ ውሳኔ በሞናኮ ሲተላለፍ ናይሮቢ አስረኛው ውድድር እንዲሰጣት ጥያቄ ለማቅረብ በስፍራው ነበሩ። ጥያቄያቸው ግን አዎንታዊ ምላሽ እንደማያገኝ የዓለም አትሌቲክስ ተንታኞች ከወዲሁ ግምታቸውን እያስቀመጡ ነው። ምክኒያታቸውም ዓለም አቀፍ ማህበሩ ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት ያለው ዝግጁ በሆነ መሰረተ ልማት ላይ እንጂ እንደ አዲስ በሚገነባ ላይ እንዳልሆነ ነው። አስረኛው ውድድር ምናልባትም ለአፍሪካ መሰጠት ካለበት የደቡብ አፍሪካዋ ፕሪቶሪያ ከተማ ከናይሮቢ በበለጠ ተመራጭ ልትሆን ትችላለች።የዓለም አትሌቲክስ ግን ከሁለቱም የአፍሪካ ከተሞች በተሻለ በአሜሪካዋ ዩጂን ከተማ መዋዕለ ንዋዩን የማፍሰስ ፍላጎት እንዳለው መረጃዎች ያሳያሉ። ምክኒያቱም ዩጂን የ2021 የዓለም ቻምፒዮናን ለማስተናገድ በኦሪገን ግዛት በሐይዋርድ ፊልድ ዩኒቨርሺሲቲ አዲስ ስቴዲየም እያስገነባች ትገኛለች። የዓለም አትሌቲክስ በዓለም ዙሪያ የልማት ስራዎችን ለማከናወን መቶ ሚሊየን ዶላር እየመደበ ይንቀሳቀሳል። አሜሪካ ከዚህ ገንዘብ እስካሁን ተቋዳሽ እንዳልሆነች የሚናገሩ ወገኖች አሁን ላይ ተራው የዩጂን እንደሚሆን ጠንካራ እምነት አላቸው። ሪድገን ‹‹አሜሪካውያን አትሌቶች ከአሜሪካ ጎዳናዎች በተሻለ በአውሮፓ ጎዳናዎች ይታወቃሉ፣ ይህ ሆን ተብሎ የተፈጠረ ባይሆንም አሁን መቀየር አለበት›› ማለታቸው አስረኛው ውድድር ለዩጂን ስለመሰጠቱ ፍንጭ ይሆናል።አዲስ ዘመን ኅዳር 22/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23446
[ { "passage": "ቦጋለ አበበ ከትንሿ አርሲ ዞን ተነስተው ከመካከለኛ እስከ ረጅም ርቀት የአትሌቲክስ ውድድሮች ዓለምን ከተቆጣጠሩ በርካታ እንቁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አንዱ ነው። የአትሌቲክስ ሕይወት አነሳሱ ትንሽ ቢሆንም፣ በታላቅ ክብርና ድሎች ታጅቦ ስሙን ከምን ጊዜም ጀግና አትሌቶች ተርታ በወርቅ ቀለም አፅፏል። በትንሽ የውድድር ዘመኑ ትልልቅ ስፖርታዊ ገድሎችን በመፈፀምም ለረጅም የውድድር ዓመታት በስፖርቱ ከቆዩ ጀግና አትሌቶች ያልተናነሰ ታሪክ ሰርቷል። የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና የማራቶን አሸናፊው ጀግና አትሌት ገዛኸኝ አበራ። ገና በአፍላ እድሜው በሬድዮ አንድ የስፖርት ዘገባ ሰምቶ ወደ አትሌቲክሱ ለመግባት የተነሳሳበት አጋጣሚ ከበርካታ ውጣ ውረዶች በኋላ ትልቅ ታሪክ ሰሪ እንዳደረገው ይናገራል። ገዛኸኝ የወደፊት የሕይወቱ እጣፋንታን ለመወሰን ‹አንድ ፈረንሳዊ ሃያ አንድ ኪሎ ሜትርን በ1፡02 ደቂቃ አጠናቆ መኪና ተሸለመ› በሚል በሬድዮ የሰማው የስፖርት ዘገባ እሱ በወቅቱ በደርሶ መልስ ሃያ አምስት ኪሎ ሜትሮችን እየተጓዘ ወደ ትምህርት ገበታው ከሚመላለስበት ሁኔታ ጋር እንዲያሰላ ጥያቄ ፈጠረበት። ‹‹ይሄ አትሌት ሃያ አንድ ኪሎ ሜትርን በዚህ ሰዓት ካጠናቀቀ እኔ ስንት ይፈጅብኛል›› ብሎም ራሱን ጠየቀ። ወደ ስፖርቱ ለመግባት የተነሳሳውም በዚህ አጋጣሚ እንደነበር በርካታ ዓመታትን ወደ ኋላ ተመልሶ ዛሬ ላይ ያስታውሳል። ገዛኸኝ በትንሽ አጋጣሚ ወደ ስፖርቱ ብቅ ቢልም እንዳብዛኞቹ የአገራችን አትሌቶች በርካታ የሕይወት ውጣውረዶችን ለማሰለፍ ተገዷል። በተለይም ከውጤት ማጣት ጋር በተያያዘ ከክለቡ እስከ መቀነስ የደረሰ ፈተና ገጥሞት እንደነበር ያስታውሳል። ዓለም ዛሬ ላይ ገዛኸኝን የሚያውቀውና የሚያስታውሰው በማራቶን ተወዳዳሪነቱ ነው። በእርግጥ ገዛኸኝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለትልቅ ስኬት የበቃው በማራቶን ነው። በሌሎች ርቀቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ውድድሮች ሲያደርግም የሚያውቀው የለም። በማራቶን የዓለምን ሕዝብ ተዋወቀ፤ በማራቶን ከስፖርቱ ጋር ተለያየ። ይህም ‹‹የማራቶን ሰው!›› አሰኝቶታል። ይሁን እንጂ ገዛኸኝ ዓለም ሳያውቀው ከማራቶን ውጪ በአገር ውስጥ ውድድሮች እንደ አስርና አምስት ሺ ሜትር ያሉ ውድድሮች ያደርግ ነበር። ታሪክ ይሰራበት ዘንድ መክሊቱን ያገኘው ግን ፈተናዎች በተጋረጡበት በአንድ አጋጣሚ ነበር። ገዛኸኝ በሚወዳደርባቸው ርቀቶች ውጤት እየራቀው ክለቡ በዚህ ምክንያት ሊያሰናብተው ሁለት ሳምንታት በቀሩት ጊዜ ከጉዳት ጋር እየታገለ ባህርዳር ላይ አንድ ውድድር አደረገ። በዚህ ውድድር ላይ ውጤት ካላስመዘገበ የፈራው አደጋ አይቀሬ ነው። ሆኖም በለስ ቀንቶት በዚህ ውድድር ሦስተኛ ሆኖ አጠናቀቀ። ይህም ከክለቡ ጋር የሚኖረውን እህል ውሃ እንዲያስቀጥል ከማድረጉ ባሻገር ብሔራዊ ቡድን በሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች አይን እንዲገባ አስቻለው። የወደፊት ዓለም አቀፍ ውድድሮች በር ተከፍቶለትም እኤአ 1999 ሎሳንጀለስ ማራቶን ላይ ተሳታፊ ሆኖ ሦስት ኬንያውያን አትሌቶችን ተከትሎ በመግባት አራተኛ ሆኖ አጠናቀቀ። ይህም እኤአ ለ1999 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና አገሩን ወክሎ እንዲወዳደር አደረገው። ሆኖም በዚያ የዓለም ቻምፒዮና አስራ አንደኛ ሆኖ በማጠናቀቁ ጥሩ የማይባል ውጤት አስመዘገበ። በዚህ ውጤት ተስፋ ያልቆረጠው ገዛኸኝ በተመሳሳይ የውድድር ዓመት በፎኮካ ማራቶን ተሳትፎ የመጀመሪያ ዓለም አቀፍ ድሉን ለማጣጣም ያገደው አልነበረም። እኤአ 2001 ና 2002 በጃፓን ምድር የሚካሄደውን የፎኮካ ማራቶን ማሸነፍ ችሏል። ከዚያም በፊት እኤአ 2000 ላይ በቦስተን ማራቶን ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል። ገዛኸኝ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ትልቅ ቦታ በሚሰጠው የሲድኒ\n2000 ኦሊምፒክም በማራቶን የማይረሳ ድል አስመዘገበ። ይህም በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ታሪክ ከማሞ ወልዴ ድል ከሰላሳ ሁለት ዓመት በኋላ በማራቶን የጀገነ አትሌት አድርጎታል። እኤአ 1932 ሎሳንጀለስ ኦሊምፒክ ከጁአን ካርሎስ ዛባላ ቀጥሎ በሃያ ሁለት ዓመቱ ወይም በትንሽ እድሜው የኦሊምፒክ ማራቶንን በማሸነፍ ሌላ የታሪክ ካባ ደርቧል። በአስራ አንድ ወራት ልዩነትም እኤአ 2001 ኤድመንተን የዓለም ቻምፒዮና ላይ በማሸነፍ ብቸኛው የዓለማችን አትሌት ለመሆን በቅቷል። እኤአ 2003 ላይ ታላቁን የለንደን ማራቶን በ2፡07፡56 ማሸነፍ የቻለው ገዛኸኝ በተመሳሳይ ዓመት ለዓለም ቻምፒዮና አገሩን ወክሎ እንዲወዳደር እድል ቢያገኝም በጉዳት ምክንያት ሳይሳተፍ ቀርቷል። ከዓመት በኋላ ባለቤቱ እልፍነሽ ዓለሙ በማራቶን አራተኛ ደረጃን ይዛ ባጠናቀቀችበት የ2004 አቴንስ ኦሊምፒክ ገዛኸኝ ኢትዮጵያን የመወከል እድል አግኝቶ ያጋጠመው ተደጋጋሚ ጉዳት ታሪክ እንዳይደግም እንቅፋት ሆኖበታል። በተደጋጋሚ የሚገጥመው ጉዳት ከዚያ በኋላ ወደ ውድድር እንዳይመለስም አድርጎታል። ገዛኸኝ ውድድር ላይ በቆየባቸው ጥቂት ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ በማራቶን ጀምሮ በማራቶን ቢሰናበትም ዘመን የማይሽረው ታሪክ አኑሯል። ብዙ የስፖርት ቤተሰቦች ገዛኸኝ ረጅም ዓመት በውድድር ላይ ቢቆይ ብዙ ታሪኮችን ይሰራ እንደነበር ያምናሉ። እሱ ግን በዚህ ብዙም አይቆጭም። ‹‹እኔ ሁለት ክብረወሰኖች አሉኝ፣ አንዱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ውጤታማነት መጥቶ ኦሊምፒክ ላይ ማሸነፍ ሲሆን ሌላኛው በአጭር ጊዜ ውድድር በማቆም ነው›› በማለት ይቀልዳል። ለብሔራዊ ቡድን የተመረጠው በማራቶን ነው፣ ውጤታማ የሆነውም በዚሁ ርቀት ነው። ሆኖም ውጤታማነቱን በቅጡ እንኳን ደጋግሞ ሳያጣጥም ጉዳት ከስፖርቱ እንዳራቀው ይናገራል። ገዛኸኝ ሌላው ቢቀር በማራቶን የዓለምን ክብረወሰን ማሻሻል በሚችልበት ወቅት በጉዳት ከውድድር ርቆ መቅረቱ የሚያስቆጫቸው ጥቂት አይደሉም። እሱ ግን ከክብረወሰን በበለጠ በርቀቱ የሰራው ታሪክ ትልቅ እንደሆነ ያምናል። አንድ አትሌት ዛሬ ተነስቶ የዓለም ክብረወሰን ቢያስመዘግብ ከዓመት በኋላ ወይም ከዚያ ባነሰ ጊዜ ሌላ አትሌት ሊሰብረው ይችላል። ክብረወሰኖች በየጊዜው ይሻሻላሉ፣ ገዛኸኝን የሚያሳስበው ግን ኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና ላይ ውጤት አምጥቶ የአገርን ስም በክብር ማስጠራት ነው። በእርግጥ ክብረወሰን ማስመዝገብ ቀላል ነገር ነው የሚል እምነት የለውም። በመገናኛ ብዙሃን ከኦሊምፒክና ከዓለም ቻምፒዮንነት በላይ ትልቅ ዋጋ ሊሰጠው እንደማይገባ ግን እምነቱ ነው። አንድ አትሌት ክብረወሰን ሲያሻሽል ገንዘብ ያገኛል፣ በገንዘቡም አገርና ሕዝብን ሊጠቅም እንደሚችል ለገዛኸኝ አይጠፋውም፣ ያም ሆኖ ለኦሊምፒክ አሸናፊ የሚሰጠው ቦታ ይበልጥበታል። በተለይም አሁን አሁን ክብረወሰን ለማሻሻል አንድ አትሌት በአሯሯጥና በቴክኖሎጂ ታግዞ ከራሱና ከሰዓት ጋር በሚፎካከርበት ዘመን በኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና ከዓለም አትሌቶች ጋር ተፎካክሮ ለውጤት የሚበቃ አትሌት ለየቅል እንደሆኑም ያስባል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቅርቡ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በስራ አስፈፃሚነት ስፖርቱን ለማገልገል ወደ ፊት የመጣው ገዛኸኝ፣ ፌዴሬሽኑን በምክትል ፕሬዚዳንትነትና የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢነት ለማገልገል እድል አግኝቷል። በርካታ የስፖርቱ ዓለም ሰዎች ከውድድር ዘመናቸው በኋላ ወደ አሰልጣኝነት ሲመጡ ቢስተዋልም ገዛኸኝ ወደ ኢንቨስትመንቱ መሰማራትን መርጧል። ወደ አሰልጣኝነት እንዳይመጣም ሁኔታዎች ተስፋ እንዳስቆረጡት ይናገራል። በተለይም እሱ ወደ አሰልጣኝነት ለመምጣት እድሉ በነበረው ወቅት በዓለም ላይ የስፖርቱ አሰልጣኝነትም ይሁን አትሌቱ በሽግግር ላይ የነበረበትና ሁኔታዎች እየተለዋወጡ የመጡበት መሆኑን ያስታውሳል። ‹‹እኔ የመርህ ሰው ነኝ፣ ለአንድ ሰው ትዕዛዝ ስሰጥ በቅንነት መንፈስ ነው፣ ያዘዝኩት ነገር ከእኔ በተሻለ እንዲፈፀም እፈልጋለሁ፣ በጣም እልኸኛ ነኝ፣ ይህን ሳስብ ከአሰልጣኝነት ጋር በተያያዘ ነገሮች እየተለወጡ ሲመጡ አስተውያለሁ›› ይላል። በተለይም አንድ አሰልጣኝ ከስር ጀምሮ አትሌቱን አሳድጎ ለውጤት በሚበቃበት ወቅት በሌሎች አሰልጣኞችና ማኔጀሮች የሚነጠቅበት ሁኔታ አሰልጣኝ ለመሆን ተስፋ የሚያስቆርጥ እንደሆነ ይናገራል። የፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ሆኖም ይህን ጉዳይ ለማስተካከል ከሌሎቹ ጋር ጥረት እንደሚያደርግ እግረመንገዱን ይጠቁማል። በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ታሪክ ከጀግኖቹ አበበ ቢቂላና ማሞ ወልዴ ቀጥሎ ገዛኸኝ በኦሊምፒክ ማራቶን ሲያሸንፍ ሦስተኛው አትሌት ነው። ከእሱ በኋላ ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ የማራቶን አሸናፊ ካገኘች ሁለት አስርት ዓመታት ተቆጥረዋል። ከማሞ ወልዴ ድል በኋላ ኢትዮጵያ ገዛኸኝን እስክታገኝ ሰላሳ ሁለት ዓመታት ተቆጥረዋል። አሁንም የገዛኸኝን ድል የሚደግም አትሌት እስኪመጣ ሰላሳ ሁለት ዓመት መጠበቅ እንደሌለበት ገዛኸኝ በቁጭት ይናገራል። ‹‹እኔ ባሸነፍኩኝ በአራት ዓመቱ ሌላ አትሌት ቢያሸንፍ ምኞቴ ነው›› የሚለው ገዛኸኝ፣ ሁል ጊዜ ከአበበና ማሞ ቀጥሎ ሦስተኛው አትሌት መባል አይፈልግም። ከእሱ ቀጥሎ አራተኛው፣ አምስተኛው ወዘተ አትሌት የሚመጣበትን ጊዜ ይናፍቃል። ‹‹ትውልድ ቅብብሎሽ ነው፣ ይብዛም ይነስም እሱ የሰራው ታሪክ ሕያው ሆኖ ይኖራል፣ የትውልድ ቅብብሎሹ እንደ አገር መቀጠል አለበት፣ የኦሊምፒክ የማራቶን ድል አንድ ቀን ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳል›› ብሎ በማመንም በፌዴሬሽን አመራርነት ዘመኑ ልምድና እውቀቱን አጣምሮ ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ እየሰራ ነው። ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ ታሪክ የገዛኸኝን የማራቶን ድል ጨምሮ አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን የሰበሰበችበት ወርቃማው የሲድኒ 2000 ትውልድ ብዙ ስራ ቢጠይቅም አንድ ቀን እንደሚደገም ገዛኸኝ ብርቱ እምነት አለው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በስፖርቱም በአትሌቱም ዘንድ ቴክኖሎጂ ያመጣቸው ችግሮች የአትሌቱን ስነልቦናና መንፈስ በመጠኑም ቢሆን ወደ ኋላ ሊጎትቱት እንደሚችሉ ቢያምንም በቁርጠኝነት ከተሰራ ችግሮችን ተሻግሮ ውጤት ማምጣት የሚቻልበት እድል እንዳለ ያስረዳል። ለዚህም ለውጥ የሚጀምረው ከራስ ነውና ሁሉም ራሱን አሸንፎ ለትውልድ አንድ አሻራ ጥሎ ማለፍ እንዳለበት ከራሱ ተሞክሮ ተነስቶ ምሳሌ ያስቀምጣል። ‹‹እኔ ወደ ስፖርቱ ስመጣ አገሬን አስጠራለሁ ብየ አይደለም፣ አትሌቲክስ እንጀራዬ ይሆናል ብዬ እንጂ፣ እኔ ራሴን ሳሸንፍ ከራሴ አልፌ ለቤተሰብ እተርፋለሁ፣ ከዚያም ለአገር›› በማለትም ምክሩን ይለግሳል። ገዛኸኝ በሕይወት ዘመኑ ይሄን ማድረግ ሲኖርብኝ አላደረኩም፣ ይሄን ማሳካት ሲኖርብኝ አላሳካሁም ብሎ ባለፈ ነገር የሚፀፀት አይነት ሰው አይደለም። ለዚህም አንድ የሕይወት ፍልስፍና ወይም እምነት አለው። ‹‹ ይብዛም ይነስም ላገኘሁት ስኬትና እውቅና ገና በእናቴ ማህፀን እንዳለሁ ፈጣሪ ያውቅ ነበር ብዬ አምናለሁ፣ ይሄን ካመንኩኝ ያደረኩትን ነገር አለማድረግ አልችልም ማለት ነው፣ ያላደረኩትን ነገር ላድርግ ብልም ማድረግ አልችልም ማለት ነው፣ ስለዚህ በሕይወቴ አላሳካሁም ብዬ የምፀፀትበት ነገር የለም›› ይላል። እኤአ ከ2003 በኋላ ከውድድር ከራቀ ወዲህ በተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተሰማርቶ ከባለቤቱ እልፍነሽ ዓለሙ ጋር ለበርካታ ዜጎች የሰራ እድል በመፍጠር አገሩን ዳግም እያገለገለ የሚገኘው ገዛኸኝ፣ ከስፖርቱ ውጪ ያለው ሕይወቱ ብዙም ሲነገር አይታይም። ብዙዎችም የሚያውቁት ሐዋሳ ከተማ በባለቤቱና በእሱ ስም ያለውን የሆቴልና ሪዞርት ኢንቨስትመንት ነው። ገዛኸኝ በቅርቡ በቢሾፍቱ ሐይቅ ዳርቻ ሃያ ሺ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሌላ ሆቴልና ሪዞርት ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ይገኛል። በአገር ውስጥም በውጪ አገርም ከባለቤቱ እልፍነሽ ጋር በመሆን ሌሎች ንግድ ስራዎች ላይ ተሰማርቶ ይገኛል።", "passage_id": "3a39c256301b1895054308d6f1f917ab" }, { "passage": " በስፖርት የመጨረሻውን ደረጃ ክብር የሚያስገኘው ውድድር ኦሊምፒክ መሆኑ ይታወቃል። በዓለም ትልልቅ ስም ያላቸው ዝነኛ አትሌቶች ሃገራቸውን ወክለው የሚሳተፉበት እንዲሁም በርካታ ክብረወሰኖች የሚሰባበሩበትም ነው። በመሆኑም በአትሌቶች ዘንድ በመድረኩ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ብቻም ሳይሆን ተሳትፎውም ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው።ኦሊምፒክ በየአራት ዓመቱ ስለሚካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት የሚደረግበት ሲሆን፤ ወጥ አቋም የሌላቸው አትሌቶች በተደጋጋሚ ኦሊምፒክ ላይ ሊታዩ አይችሉም። በመሆኑም በርካታ ተሳትፎ ያላቸው አትሌቶችን ለማግኘት አዳጋች ነው። እንግሊዛዊቷ አትሌት ግን በመጪው ዓመት ስድስተኛ የኦሊምፒክ ተሳትፎዋን ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኗን ነው ያሳወቀችው። በተለይ ለወጣት አትሌቶች አስተማሪ የሆነ ተሞክሮዋንም ለቢቢሲ አጋርታለች።ጆ ፓቬ አምስት አሊምፒኮች ላይ የተሳተፈች አንጋፋ አትሌት ስትሆን በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስድስተኛ ተሳትፎዋን በማድረግ የክብረወሰን ባለቤት ለመሆን ፍላጎት አላት። ከዚህ ቀደም የሃገሯ ልጅ የሆነችው ጦር ወርዋሪ ቴሳ ሳንደርሰን ስድስት ኦሊምፒኮች ላይ ሀገሯን የወከለች አትሌት በመባል ተመዝግባለች። ፓቬ ስድስተኛዋን ተሳትፎ የምታደርግ ከሆነ ደግሞ በመም አትሌት የመጀመሪያዋ ትሆናለች።\nፓቬ እአአ በ2014 ከወሊድ በኋላ በአውሮፓ ሻምፒዮና በ10ሺ ሜትር ስትሳተፍ በአንጋፋነቷ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆና ነበር። ይሁን እንጂ በ40ዓመቷ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆን ብቃቷን ማስመስከር ችላለች። በቶኪዮው ኦሊምፒክ ስትሳተፍም ዕድሜዋ 46 ስለሚሆን ምናልባትም በኦሊምፒኩ አንጋፋዋ አትሌት ልትሆን ትችላለች። ፓቬ ለቢቢሲ በሰጠችው አስተያየት ላይም «ዕድሜዬን ረስቼ ስድስተኛውን የኦሊምፒክ ተሳትፎዬን አደርጋለሁ» ብላለች።አትሌቷ ሃገሯን ወክላ በኦሊምፒክ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው እአአ በ2ሺ በተካሄደው የሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ ነበር። «በቶኪዮ የሚካፈለው ብሄራዊ ቡድን ጥሩ ተፎካካሪ እንዲሆን እፈል ጋለሁ። በመሆኑም ዝግጅታችንን ቀድመን መጀመር ይገባናል፤ ፉክክሩ ደግሞ ይበልጥ ደስ የሚያሰኝ ነው» ብላለች። የሁለት ልጆች እናት የሆነችው አትሌቷ ከኦሊምፒኩ አስቀድሞ በዘንድሮው የዶሃ ዓለም ሻምፒዮና አቅሟን የመፈተሽ ፍላጎት እንዳላትም ጨምራ ገልጻለች። እአአ በ2017 በለንደን በተካሄዱት ሁለት ትልልቅ የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ ብትሆንም አልተሳካላትም ነበር። በለንደን ማራቶን ውድድሯን ሳታጠናቅቅ አጋማሽ ላይ ስታቋርጥ፤ በ10ሺ ሜትር በተካፈለችበት ሻምፒዮና ደግሞ በጉዳት ምክንያት ውድድሯን ለማጠናቀቅ አልቻለችም ነበር።ያለፈው ዓመት በተካሄደ ሌላ ውድድር ግን በረጅም ርቀት የመም ላይ ውድድር ሶስተኛ በመሆን የነሃስ ሜዳሊያውን ወስዳለች። በባለቤቷ የምትሰለጥነው አትሌቷ በልምምድ ቦታዎች ላይም ነፍስ ያላወቁ ልጆቿን ይዛ ትሄዳለች «ሩጫ እወዳለሁ፤ የአእምሮ እና ሰውነት ጤናን ለማግኘት ያግዛል። ከቤተሰብህ ጋር ሆነህ ስትከውን ደግሞ ይበልጥ መነሳሳትን ይፈጥራል። ባለቤቴ ያግዘኛል፤ ሥራችንን የምንሰራውም እንደ ቡድን ነው። ሯጭ ስትሆን መጨናነቅን ማስወገድ የግድ ነው ይህም የአእምሮን ጤና ይሰጣል። እድሜህንም እንደ ልምድ መጠቀም ትጀምራለህ» ስትልም የህይወት ልምዷን ታጋራለች።የአትሌቷ የኦሊምፒክ ተሳትፎ በተለያዩ ችግሮች የታጀበ ይሁን እንጂ ተስፋ አለመቁረጧ ግን ለብዙዎች ተሞክሮ የሚሆን ነው። እአአ 1997 ከባድ የሆነና ውስብስብ ቀዶ ጥገና የሚያስፈልገው የጉልበት ጉዳት የደረሰባት ቢሆንም፤ ከዚያ አገግማ በሲድኒ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። እአአ በ2004ቱ የአቴንስ ኦሊምፒክ ከመሳተፏ ሶስት ወራት በፊት የጡንቻ ጉዳት ቢደርስባትም አምስተኛ ደረጃ በመያዝ የዲፕሎማ ተሸላሚ ነበረች።በ2008ቱ የቤጂንግ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሯን ያጠናቀቀችው ደግሞ በውድድሩ ዋዜማ በምግብ መበከል የጤና መታወክ ስለደረሰባት ነበር። በሀገሯ በተዘጋጀው የ2012 ኦሊምፒክ በ5 እና 10ሺ ሜትር ውድድሮች ተሳትፎዋ ሰባተኛ ደረጃ በመያዝም የመጀመሪያዋ አውሮፓዊት አትሌት ተሰኝታለች። በሪዮ በተካሄደው የ2016ቱ ኦሊምፒክ ደግሞ ዘግይታ ውድድሩን በመጀመሯ በ10ሺ ሜትር 15ኛ ደረጃን ነበር የያዘችው። «የሪዮ ኦሊምፒክ ተሳትፎዬ በጣም አስደሳች ነበር፤ አብረውኝ የሮጡት አትሌቶችም ከእኔ በ20ዓመት የሚያንሱ ነበሩ። ቢሆንም ሁሌም ሃገሬን መወከል ለእኔ ኩራት ነው» ስትልም ትገልጻለች።አዲስ ዘመን ጥር 13/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "121a3477a1e1f36d985d4b50ab4afece" }, { "passage": "ድልን ለማብሰር ከማራቶን እስከ አቴንስ የሮጠው ግሪካዊው መልዕክተኛ ፊሊፒደስ፣ በባዶ እግሩ 42 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ለጥቁሮች ኩራት ለዓለም ህዝብ ትንግርት የሆነው አበበ ቢቂላ፣ ለጥቁሮች መብት ትግል ከኦሊምፒክ ስኬት ይልቅ ሰብዓዊነትን ያስቀደመው ቦክሰኛው መሃመድ አሊ፣ በቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት በእንብርክክ ተማጽኖው የአምስት ዓመታትን የእርስ በእርስ ግጭት ማብቂያ ያበጀለት የእግር ኳስ ፈርጥ ዲድየር ድሮግባ፣… ዓለም ካከበራቸው ታሪክም ከጀግኖች መዛግብት ካሰፈራቸው ስፖርተኞች ጥቂቶች ናቸው። ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ወዲህ ስፖርት በሰው ልጅ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ውስጥ ሰፊውን ድርሻ መያዙ ገሃድ ነው። በዚህ ተወዳጅ ክንዋኔ ላይም በጦርነት አውድ ከሚዋደቁት ባላነሰ በርካታ ጀግኖች ተፈጥረው አልፈዋል፤ በዚህ ዘመንም እየተፈጠሩ ይገኛሉ። ስፖርተኞች ደረታቸውን ለጥይት ነፍሳቸውንም ለአገራቸው መገበር ባይጠበቅባቸውም፤ በእልህ አስጨራሽ ትግል ነጭ ላባቸውን አፍስሰው በሚያገኙት ድል ግን አገራቸውን ያስጠራሉ፣ ባንዲራቸውንም በማውለብለብ ህዝባቸውን ያኮራሉ። ታሪክም ከራሳቸው ይልቅ ህዝባቸውን ያስቀደሙ፤ ራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠውም አገራቸውን ያስጠሩትን እነዚህን ጀግኖች እያነሳ ሲዘክራቸው ይኖራል። ለዛሬም ከጀግና ስፖርተኞች መካከል አንዱን 100 ዓመታትን ወደኋላ ተመልሰን እናስታውስ። በአገረ አሜሪካ ከታዩ ስፖርተኞች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል፤ ጂም ትሮፔ። በኦሊምፒክ ተሳትፎው ያሳየው ቁርጠኝነት አገር ወዳድነቱን የመሰከረ ሲሆን፤ ተግባሩም ለብዙዎችም ትምህርት ሆኗል። እርግጡን የሚያወሳ የልደት የምስክር ወረቀት ባይገኝም አሁን ኦክለሃማ ከተሰኘው የአሜሪካ ግዛት እ.አ.አ በ1887 እንደተወለደ በህይወት ታሪኩ ተጠቅሷል። ትሮፔ በልጅነቱ ከባድ እና ውስብስብ የሆነ ቤተሰባዊ ህይወት የነበረው ሲሆን፤ የመንትያ ወንድሙ እናቱ እንዲሁም የአባቱ ሞት ደግሞ የልጅነት ህይወቱን ይበልጥ ፈታኝ ሊያደርግበት ችሏል። ትምህርቱን ለበርካታ ጊዜ እያቋረጠ እና እየቀጠለ ቢቆይም፤ ፔንሲልቫኒያ በሚገኝ የኢንዱስትሪ ትምህርት ቤት ተማሪ በነበረበት ወቅት ስፖርታዊ ተሳትፎውን ጀምሯል። እንደ እድል ሆኖም በወቅቱ በአሜሪካ ስመጥር በሆኑት የእግር ኳስ አሰልጣኝ ግሌን ስኮቤይ የመሰልጠን አጋጣሚ ተፈጥሮለት ነበር። ነገር ግን በዚያው ዓመት አሰልጣኙ ከዚህ ዓለም በማለፋቸው ከስፖርት ሊርቅ የግድ ሆነበት፤ ከዓመታት በኋላ ኮሌጅ እስኪገባ ድረስም በድጋሚ ወደ ስፖርት አልተመለሰም ነበር። ወደ ስፖርት ከተመለሰ በኋላም በእግር ኳስ እና ቤዝቦል ስፖርቶች ባሻገር በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች መሳተፍ ብቃቱ ተደናቂ አድርጎት ቆይቷል። ከኮሌጅ ቡድን እስከ ክለቦች ድረስም በተለያዩ ውድድሮች ላይ ተሳትፎ ሻምፒዮን ለመሆን ችሏል። በእግር ኳስ ስፖርት የነበረው ብቃት በተለይ የሚደነቅ ይሆን እንጂ በአትሌቲክስ ስፖርቶች ላይ የሚያሳየው ችሎታ ግን የሚያስገርም ነበር። ይህንን ተከትሎም እ.አ.አ በ1912 የስዊድኗ ስቶኮልም አዘጋጅ ለሆነችበት ኦሊምፒክ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድንን ከሚወክሉት መካከል አንዱ በመሆን ተመረጠ። ወቅቱ የፔንታቶሎን እና ዴክታቶሎን የውድድር ዓይነቶች በኦሊምፒክ የተካተቱበት እንደመሆኑም ቶርፔ የታጨው ለእነዚህ የውድድር ዓይነቶች ነበር። የውድድሩ ዕለት ደርሶም ቶርፔ አስደማሚ ብቃቱን ለዓለም ሊያሳይ ሰዓታት ብቻ ቀሩት። ነገር ግን የእዚያን ዕለት ጠዋት ከእንቅልፉ ሲነቃ ጫማውን ካስቀመጠበት ሊያገኝ አልቻለም፤ ከፍለጋ በኋላም እንደተሰረቀ አወቀ። በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ መሳተፍ በግሉ ከሚያስገኝለት ክብር በላይ አገሩን መወከል የዜግነት ግዴታው በመሆኑ ተስፋ መቁረጥ የማይታሰብ ነው። በመሆኑም በአጋጣሚው ከመቆጨት ይልቅ አማራጭ ፍለጋውን ተያያዘው። ከቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቅርጫት ውስጥም አገልግሎት የማይሰጡ ሁለት የተለያዩ ጫማዎችን አገኘ። የውድድር ሰዓቱ እየደረሰ በመሆኑም ጫማዎቹን ሳያቅማማ ለካቸው። አንዱ ጫማ ለእርሱ የማይሆን ሰፊ መሆኑ ሌላ ችግር ነበር። ምን ማድረግ እንዳለበትም አሰበ፤ ያገኘው መላም ሰፊውን ጫማ በሁለት ካልሲዎች ደራርቦ ማድረግ ነበር፤ እናም አደረገው። የእርሱ ባልሆኑት ሁለት ዓይነት ጫማዎችን በነጭ እና ጥቁር ካልሲዎች ተጫምቶም ወደ ውድድር ስፍራው አመራ። በተሳተፈባቸው ሁለት ውድድሮችም ብቃቱን አስመሰከረ። ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለማጥለቅ በቃ። በፔንታቶሎን (ርዝመት ዝላይ፣ ዲስከስ ውርወራ፣ አጭር ርቀት ሩጫ እንዲሁም ትግል) ካደረጋቸው አምስት ውድድሮች መካከል አንዱን ብቻ ተሸንፎ (በጦር ውርወራ) በሰበሰባቸው ነጥቦች ብልጫ አሸናፊ ሊሆን ችሏል። በተሳተፈባቸው የፔንታቶሎን እና ዴክታቶሎን 15 ውድድሮች በድምሩ ስምንቱን በማሸነፍም የቁጥር አንድነትን ማዕረግ ለመጎናጸፍ ችሏል። ቶርፔ በወቅቱ በውድድር አሸናፊነቱ ካጠለቃቸው ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎች ባሻገር ሌሎች ሁለት ሽልማቶችንም ተቀዳጅቷል። የመጀመሪያው ገጸ- በረከት\nበውድድር አዘጋጇ አገር ስዊድን ንጉስ ጉስታቭ አምስተኛ እጅ የተበረከተለት ሲሆን፤ «የዓለም ምርጡ አትሌት ነህ» በማለትም አበረታተውታል። የሩሲያው ኒኮላስ ሁለተኛም ለትሮፔ ሁለተኛውን የማበረታቻ ሽልማት ሰጥተውታል። ነገር ግን ይህ ታሪክ በጋዜጦች ታትሞ ለንባብ የበቃው ትሮፔ ገድሉን ከፈጸመ ከ36 ዓመታት\nበኃላ እ.አ.አ በ1948 ነበር።\nመጽሐፍትም በስሙ ተጽፈው ገበያ ላይ የዋሉት እ.አ.አ በ1952 ነው።\nአትሌቱ ከዓመታት በኋላ በዓለም ላይ ታዋቂ መሆኑ በአሜሪካ ዜጎች ልብ ሰፊ ቦታ አላሳጣውም፤ አሁንም ድረስ ብዙዎች «ጀግናችን» ሲሉ ያወድሱታል። በፔንሲልቫኒያ ግዛትም በስሙ «ጂም ቶሮፔ» በሚል የተሰየመ ከተማ አለው።አዲስ\nዘመን ሚያዚያ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "18c14ba7775635036928a87643636857" }, { "passage": "ነገር ግን የድል ዜናው ቦታውን ቀይሮ በተገናኙባቸው ውድድሮች ኬንያዊው አትሌት የርቀቱ ፈጣን ተሰኘ፡፡ በጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቆ የቆየው የሃገር አቋራጭ ንጉሱ ቀነኒሳም በርቀቱ ያለውን ተስፋ ከማሳየት በቀር ለሁለት ዓመታት ውጤት አላስመዘገበም ነበር፡፡ እአአ 2016 ግን የፓሪስ ማራቶንን በማሸነፍ በጠባብ የደቂቃዎች ልዩነት ሁለተኛው የርቀቱ ፈጣን አትሌት ለመሆን ችሏል፡፡ በቀጣዩ ዓመት በለንደን ማራቶን ያስመዘገበው ሰዓት ከፈጣኑ የዘገየ መሆኑ በርቀቱ ያለውን ተስፋ አጠራጣሪ አድርጎት ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በ5 እና 10ሺ ሜትር የሶስት ጊዜ የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑ ቀነኒሳ የባት ፣ የቁርጭምጭሚት፣ ተረከዝ፣ ሽንጥ እና ቋንጃ ጉዳቶች ጋር ትግል ሲያደርግ በመቆየቱ ነው፡፡ የአትሌቱ የረጅም ጊዜ ማኔጀር ጆስ ሄርሜንስም ስለ ቀነኒሳ ከሰሞኑ በዓለም አትሌቲክስ ድረ ገጽ አጠቃላይ መረጃ ሰጥቷል፡፡ አሰልጣኙ አትሌቱ የነበረበትን ሁኔታ ሲገልጽም ‹‹በአዲስ አበባ ያለው ህይወቱ ውጥረት የበዛበት በመሆኑ ለልምምድ እንዲሁም ለማገገም የተመቸ ጊዜ የለውም፡፡ ከሩጫው ባሻገር በቢዝነስ ስራዎችም ላይ ተሳታፊ እና የልጆች አባት እንደመሆኑም አብዛኛውን ጊዜውን በዚህ ያሳልፋል፡፡ በዚህ ሂደትም ጊዜውን ያለእረፍት እያሳለፈ ነበር›› ሲልም ይገልጻል፡፡ ‹‹የማራቶን ሁለተኛውን ሰዓት ካስመዘገበበት የበርሊን ማራቶን ሁለት ወራት አስቀድሞም ለጥቂት ጊዜ ከውጥረት መላቀቅ እንዳለበትና ጥሩ የማገገሚያ ጊዜ እንደሚኖረው አስረዳነው›› ይላል ማኔጀሩ፡፡ ይህን ማሳመን ቀላል ባይሆንም በመጨረሻ ግን ከቤተሰቦቹ ተለይቶ ለሁለት ወራት በሆላንድ በምትገኝ አንዲት ከተማ ለማሳለፍ የግድ ሆነ፡፡ አትሌቱም የሩጫ ህይወቱን ከማቋረጡ አስቀድሞ በማራቶን አንድ ታሪክ ማስመዝገብ የሚፈልግ በመሆኑ ከጉዳቱ በቶሎ አገግሞ ወደ ልምምድ እንዲገባ የቻሉትን ሁሉ ማድረጋቸውን ማኔጀሩ ያስታውሳል፡፡ ክብደቱ በመጨመሩም በሆላንዳዊው የስነ ምግብ ፕሮፌሰር አርማንድ ቤቶንቬል እገዛ የአመጋገብ ሁኔታውን ማስተካከል ተችሏል፡፡ በአዲስ አበባ ቆይታው የአመጋገብ ሁኔታው የተጠና አልነበረም፤ አብዛኛውን ጊዜ የሆቴል ምግብ የሚያዘወትር ከመሆኑ ጋር በተያያዘ እንደ አትሌት በሚጠበቅበት ሁኔታ ላይ አልነበረም፡፡ በባለሙያዎቹ አማካኝነትም ፕሮቲን፣ ሩዝ እና ድንች በተሻለ ሁኔታ እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ ስልጠናውንም በአግባቡ ነበር የሚከታተለው፡፡ ወደ ዋናው ስልጠና ከገባም በኃላ በሳምንት እስከ 50 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ጥሩ የሚባል ጊዜ አሳልፏል፡፡ የመልካም አስተሳሰብ ባለቤት በመሆኑም ከታሰበው በተሻለ ፍጥነት መሻሻል ሊያሳይ ችሏል፡፡ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኃላም በአሰልጣኝ ሃጂ አዲሎ ስር በመሆን ስልጠናውን ሳያዘባ ሲሰራ ስለ ነበር በጥቂት ጊዜ ወደ ቀደመ አቋሙ ሊመለስ ችሏል፡፡ ዝግጅቱ በርቀቱ ከፈጣኖች ተርታ ከሚሰለፈውና ከዓለም ቻምፒዮኑ አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ ጋር መሆኑም የተሻለ ነገር አስገኝቶለታል የሚል እምነት እንዳላቸው ኸርሜንስ ይናገራሉ፡፡ በእርግጥ ስልጠናውን በሚያደርግበት ወቅት አዲስ አበባ ዝናባማ የአየር ሁኔታ ነበራት፤ ይህም አስቸጋሪ ስለነበር ስልጠናውን በበፊቱ ልክ ማከናወን አንዳልተቻለም አልዘነጉም፡፡ ‹‹ውድድሩ ሲቃረብም በአትሌቱ ብቃት ሁላችንም ከመተማመን ላይ ደርሰን ነበር፡፡ እኛ በስልጠናው ወቅት ሲያሳይ በቆየው ብቃት ከፍተኛ ተስፋ ስንሰንቅ እርሱ ደግሞ በጥሩ ውጤት ማጠናቀቅን አላማው አድጎ ነበር፡፡ ከሚታመነው በላይ ጠንካራ አትሌት ነው፤ በውድድሩ ላይ ኬንያዊው አትሌት ከያዘው ክብረወሰን በሁለት ሰከንዶች ብቻ ዘግይቶ ገብቷል›› በማት አ ድ ና ቆ ታ ቸ ው ን ይገልፃሉ፡፡ እውቅና ያልተሰጠውና ሰው ሰራሽ በሆነ መንገድ ቢሆንም የሰው ልጁ 42ኪሎ ሜትሮችን ከ2ሰዓት በታች መግባት ይችላል የሚለው ሙከራ በኬንያዊው ኪፕቾጌ እውን ከተደረገ በኃላም የስፖርት ቤተሰቡ ጥያቄ ተመሳሳይ ሆኗል፡፡ ‹‹ቀጣዩ ምንድነው?›› የሚለው ፤ ምላሹም ቀነኒሳን ከማየት የተሻለ አለመኖሩን የሚያሳይ ነው፡፡ ቀነኒሳ ማራቶንን በተለመደው መንገድ ሮጦ በቴክኖሎጂ ሳይታገዝ ከ2፡00 በታች መሮጥ እንደሚችል በቅርቡ አብሮ እየሰራ የሚገኘው አሰልጣኙ ሃጂ አዲሎም በቅዳሜው እለት እትማችን ባደረጉት ቃለ ምልልስ መግለፃቸው ይታወቃል፡፡ አሰልጣኙ ሃጂም ‹‹ ቀነኒሳ ሩጫ ከማቆሙ አስቀድሞ ማራቶንን ከ2፡00 በታች ይሮጣል፣ በየትኛው ውድድር እንደሚሆን ግን መናገር አይቻልም›› ይላሉ፡፡ ቀነኒሳ ምናልባትም ይህን ለማሳካት የቀጣዩን ዓመት የበርሊን ማራቶን መታገስ ላይጠበቅበት ይችላል፡፡ በቀጣዩ ሚያዝያ በለንደን ማራቶን ለመሳተፍ በሆላንድ አገር የሚያደርገው ዝግጅት በታሰበው ልክ ከሄደ ህልሙን በቅርቡ እውን ሊያደርግ እንደሚችል ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 15/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "fa3b2da7adfb2e87723b00e9316e3be8" }, { "passage": "ታላቋ አህጉር አፍሪካ ብዙ ጊዜ በስፖርት መድረክ ታላላቅ አውራ ውድድሮችን የማዘጋጀት እድል ሲገጥማት አይስተዋልም። ለዚህም ከአቅምና ሌሎች ተያያዥ ችግሮች ጋር ተያይዞ አህጉሪቱ እንደማትችል አድርጎ መቁጠር ዋናው ምክንያት ነው። እኤአ 2010 ላይ ደቡብ አፍሪካ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫን በተሳካ ሁኔታ ካስተናገደች ወዲህ ይህ የተሳሳተ አመለካከት በጥቂቱም ቢሆን ተስተካክሏል ማለት ይቻላል። ለዚህም እንደ ሞሮኮ ያሉት አገራት በቅርቡ የዓለም ዋንጫን ለማስተናገድ ካደጉት አገራት ጋር ጨረታ ውስጥ ሲገቡ ለማየት ተችሏል።ኦሊምፒክ የዓለማችን ትልቁ የስፖርት መድረክ እንደመሆኑ መጠን አፍሪካውያን በተሳትፎ እንጂ በአዘጋጅነት ምን እንደሚመስል ተመልክተውት አያውቁም። አሁን ግን ይህን ታላቅ መድረክ በራሳቸው ምድር ደግሰው ሌሎችን የሚጋብዙበት መንገድ እየተጠረገ የመጣ ይመስላል። ለዚህም ከትናንት በስቲያ ዋናውን የኦሊምፒክ ውድድር ባይሆንም ሴኔጋል ቀጣዩን የወጣቶች ኦሊምፒክ እንድታዘጋጅ መመረጧ ማሳያ ነው። በአርጀንቲና ቦነ ሳይረስ በተካሄደው ሰላሳ ሦስተኛው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ሴኔጋል እኤአ በ2022 የሚካሄደውን አራተኛውን የወጣቶች ኦሊምፒክ ለማዘጋጀት በሙሉ ድምጽ የምርጫ ውጤት በይፋ ተረክባለች።በዘመናዊው ኦሊምፒክ 122 ዓመታት የውድድር ታሪክ አዘጋጅነትቱ ወደ አፍሪካ አህጉር ሲመጣ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ ሴኔጋል ይህንን እድል ያገኘችው ከሌሎች ሶስት የአፍሪካ ሀገራት ማለትም ከቱኒዚያ፡ ናይጄሪያ እና ቦትስዋና የቀረበባትን ከባድ ፉክክር አሸንፋ እንደሆነም ተገልጿል፡፡በእለቱ የሀገራቸውን ለዚህ ውድድር መመረጥ እና ሀላፊነቱን በአካል ለመቀበል በቦነ ሳይረስ ጉባኤ የተገኙት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል ሀገራቸው ለዚህ ውድድር ሲባል አዲስ የተገነባች ከተማን ጨምሮ ለውድድሩ ሶስት ከተሞችን በማዘጋጀት በወጣቶች ብዛት ቀዳሚ የሆነችውን አህጉራቸውን አፍሪካን የሚያኮራ ዝግጅት እንደሚያዘጋጁ ተናግረዋል። ለዚህ ውድድር ሲባልም አዳዲስ ዘመናዊ ባቡሮችና ሃምሳ ሺ ሰው የሚይዝ ስቴድየም ለመገንባት እንደታሰበ ታውቋል።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አፍሪካ የኦሊምፒክ ውድድሮችን እንድታዘጋጅ ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ፍላጎት የነበረው ሲሆን ከወራት በፊት ደቡብ ኮሪያ ፒዮንግያንግ ተዘጋጅቶ የነበረውን የክረምት ወራት ኦሊምፒክ አፍሪካ እንድታዘጋጅ ፍላጎት እንደነበረው ይታወሳል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ይህ እድል ለአፍሪካ መሰጠቱ ወደ ፊት ዋናውን የበጋ ወራት ኦሊምፒክ በአፍሪካ ለማዘጋጀት እድል እንደሚፈጥር በመናገር «ጊዜው የአፍሪካ ነው» ብለዋል።ሦስተኛው የዓለም ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታዎች በአርጀንቲና መዲና ቦነ ሳይረስ በታላቅ ድምቀት ከትናንት በስቲያ ተጀምሯል። ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ የመክፈቻ ስነ ስርዓቱ በስታዲየም ውስጥ ሳይሆን ሁሉም ህብረተሰብ ሊመለከተው በሚችል በከተማዋ አደባባይ ላይ ነበር። ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ206 ሀገሮች የተውጣጡ አራት ሺ አትሌቶች በሰላሳ ሁለት የስፖርት አይነቶች ለአስራ ሦስት ቀናት ያህል ይፋለማሉ። ኢትዮጵያ በዚህ መድረክ በአትሌቲክስና ብስክሌት ስፖርቶች ተሳታፊ ነች።ይህ የቦነስ አይረስ የወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታዎች በኦሊምፒክ የውድድር ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የወንድና የሴት ተሳታፊ አትሌቶች ቁጥር እኩል የሆነበትና በቶኪዮ 2020 የአዋቂዎች ኦሊምፒክ ላይ ሊካተቱ ይችላሉ የተባሉ እንደ ድብልቅ ጾታን የሚያካትቱ የውድድር አይነቶች የሙከራ ውድድር የሚደረግበት ነው።የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ስምንተኛው ፕሬዚዳንት ጃክ ሮጅ ሃሳብና ውጤት የሆነው እድሜያቸው ከ15-18 ያሉ ወጣቶች ብቻ የሚሳተፍበት የወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ እ.ኤ.አ 2010 ሲንጋፖር ላይ የተጀመረ ሲሆን፤ ዋነኛ አላማው በሀገራት መካከል ውድድሮች ገዝፈው ሜዳሊያዎችን መሰብሰብ ሳይሆን ወጣቶችን በስፖርት እንዲሳተፉ ማነሳሳት፣በኦሊምፒክ እሴቶች ላይ የተመሰረተ ኑሮ እንዲኖሩ ማበረታታት እና የኦሊምፒዝም ፍልስፍና አምባሳደር እንዲሆኑ ማድረግ ነው። እነዚህ አምባሳደሮች ተቀራርበው የየሀገራቸውን ባህል፣ትውፊትና እና ወግ የሚከፋፈሉበት ብሎም በልዩነታቸው ውስጥ አንድነታቸው ጎልብቶ በኦሊምፒዝም አተያይ ተቻችለው እና ተከባብረው ይህችን ዓለም የተሻለችና ተፈቃቅረው የሚኖሩባት ሰላማዊ መንደር ማድረግ ነው፡፡ይህንን አላማ አንግቦ ሲንጋፖር ላይ የተጀመረው የዓለም ወጣቶች ኦሊምፒክ ለሁለተኛ ጊዜ በቻይና ናይንጄ ላይ ተካሂዲ ተራውን ለአርጀንቲናዋ መዲና ቦነስ አይረስ መስጠቱ ይታወቃል።ሀገራችን ከዚህ ቀደም በተካሄዱት ሁለቱም ጨዋታዎች ተሳትፋ ጥሩ ውጤት ያገኘችበትና ተስፋ የሚጣልባቸው እንደነ ዮሚፍ ቀጄልቻ ተተኪ አትሌቶችን ለማየት የቻለችበት ሲሆን በዚህ በሶስተኛው የወጣቶች ኦሊምፐክ ጨዋታ ላይም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ጠንከር ያለ ዝግጅት አድርጋ ወደ ስፍራው ልዑካኗን ልካለች፡፡ቦጋለ አበበ", "passage_id": "c21f3356fd566e8d1a52d650e25e5cd5" } ]
91be22f70cde65b2bccfc64d43ce501a
c2238b1ce8e1b5913331d36b61cd1d5e
ኢትዮጵያውያን በድልና በክብረወሰን የደመቁበት የቫሌንሲያ ማራቶን
‹‹ስፖርታዊ ጨዋነት ለሰላማዊ ውድድር›› በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የውይይት መድረክ በሀዋሳ ተካሄደ፡፡ በውይይቱ የደቡብ ክልል መስተዳድር ፕሬዚዳንት አቶ ርዕስቱ ይርዳው፣ የኢፌዴሪ ባህል ፣ ቱረዝምና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴታ አቶ ሀብታሙ ሲሳይ፣ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤልያስ ሽኩር፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የክልሉ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ የሺዋስ ዓለሙና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች መገኘታቸውን የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ አመልክቷል፡፡ በውይይቱ ከፕሪሚየር ሊግ፣ ከብሔራዊ ሊግና ከፍተኛ ሊግ የመጡ አሰልጣኞች፣ ሥራ አስኪያጆች፣ ቡድን መሪዎች፣ ቴክኒካል ዳይሬክተሮችና የክልሉ ዞኖች ስፖርት ዘርፍ ሃላፊዎች፣ የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። በ2012 ዓ.ም በክልሉም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች የፍቅር፣ የአንድነት፣ የሰላምና የመቻቻል እንዲሆኑ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አቶ ርዕስቱ ይርዳው ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሮችን የሁከትና የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ የሚፈልጉ አካላትን መታገልና መስመር ማስያዝ ጊዜ የሚሰጥ ጉዳይ አለመሆኑን የተናገሩት አቶ ርዕስቱ ችግር በሚፈጥሩት አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድም አብራርተዋል፡፡ የአካል ጉዳተኛ ስፖርት ባለሙያዎች ስልጠና ለአካል ጉዳተኛ ስፖርት ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በአዳማ እየተሰጠ ነው። አካል ጉዳተኞች በስፖርታዊ እንቅስቃሴ ተሳታፊና እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ ሊፈጠርላቸው እንደሚገባ በስፖርት ፖሊሲው የትኩረት አቅጣጫ ላይ በግልፅ ሰፍሯል። ይህን ተግባራዊ ለማድረግ በተለይም የአካል ጉዳተኛ የህብረተሰብ ክፍሎችን በስፖርት ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ በተለያየ ጊዜ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች፣ ስልጠናዎች እንዲሁም የውድድር መድረኮች ሲፈጠሩ ቆይተዋል። ትናንት የተጀመረው ስልጠናም በፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ከኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ፌዴሬሽንና ከኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ ኮሚቴ ጋር በመተባበር ለፖራሊምፒክና መስማት ለተሳናቸው ስፖርት ባለሙያዎች በስርዓተ ፆታና በአመራርነት ዙሪያ የተዘጋጀ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መሆኑን የስፖርት ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል፡፡ ስልጠናው ለተከታታይ 3 ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ከ60 በላይ ሙያተኞች ተሳትፈዋል። ስልጠናውን ከሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ በመጡ ባለሙያዎችና ከኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ፌዴሬሽን ባለሙያዎች አማካኝነት እየተሰጠም ይገኛል። በሳምንቱ መጨረሻ በተካሄዱ የጎዳና ላይ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል። የዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ በሰጠውና በስፔኗ ቫሌንሲያ በተካሄደው ውድድር ላይ በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ቀዳሚውን ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል። በተለይ በሴቶች ምድብ በተካሄደው ውድድር በጎረቤት አገር ኬንያ አትሌቶች ጋር እስከ 10ኛው ኪሎ ሜትር ድረስ የአንገት ለአንገት ትንቅነቅ በተካሄደበት ውድድር ኢትዮጵውያን ባልሸነፍ ባይነት እስከ መጨረሻ ታግለው ድሉን የግላቸው ማድረግ ችለዋል። በውድድሩ እስከ 15 ኪሎ ሜትር ድረስ ሁለት አትሌቶች ወደ ፊት መውጣት ቢችሉም በማሬ ዲባባና ቪቪያች ቼሮይት መካከል የነበረው አስገራሚ ፉክክር ሩጫውን ከመነሻውም አጓጊ አድርጎታል። ከዚያ በኋላ ባሉት ኪሎ ሜትሮችም ኢትዮጵያ ውያኑ ሮዛ ደረጀ ፣ አዝመራ አብረሃና ብርሃኔ ዲባባ እየተፈራረቁ በመምራት ለኬንያውያኑ ፈታኝ መሆን ችለዋል። በነበረው ጠንካራ ፉክክር አትሌቶቹ የርቀቱን ግማሽ የሸፈኑበት ሰዓትም ፈጣን እንደነበር ለመታዘብ ተችሏል።፡ ከ40ኛው ኪሎ ሜትር በኋላ ሮዛ ደረጃ የበላይነቱን ብትይዝም በኬንያዊቷ አትሌት ብርቱ ፉክክር ገጥሟት ነበር። ሆኖም አዝመራ አብረሃ ተጭና በመሮጧ ምክንያት ሮዛ ወደ ፊት ለመውጣት ስታደርግ የነበረውን ጥረት እንዲሳካ አድርጋለች። በቅርቡ በተካሄደው የለንደን ማራቶን ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው ሮዛም ባገኘችው ዕድል በመጠቀም ርቀቱን በቀዳሚነትና የቦታውን ክብረ ወሰን በማስመዝገብ ጭምር ለማጠናቀቅ ችላለች። የገባችበት ሰዓትም 2:18:30 ሆኖ ሲመዘገብ ቀድሞ ከነበራት ፈጣን ሰዓት በ47 ሰከንዶች የፈጠነ ሆኗል። ሮዛ ያስመዘገበችው ሰዓት በርቀቱ ቀዳሚ ከሆኑ አስር ባለ ፈጣን ሰዓት አትሌቶች መካከል እንድትካተት አስችሏታል። በርቀቱ ለድሉ መገኘት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራት የ21 ዓመቷ ወጣት አትሌት አዝመራ አብረሃ ደግሞ ጠባብ በሆነ ልዩነት 2:18:33 የሆነ ሰዓት በማስመዝብ ሁለተኛ በመሆን ውድድሩን ፈጽማለች። የድሉ ባለቤት የሆነችው ሮዛ በስፔን አገር ላይ ሮጣ ስታሸንፍ ይህ የመጀመሪያዋ አይደለም። በዚሁ ዓመት ከወራት በፊት አትሌቷ በባርሴሎና በተካሄደ ግማሽ ማራቶን 1:06:01 የሆነ ሰዓት በማስመዝገብ ቀዳሚ ሆና ማጠናቀቋ ይታወሳል። ሁለተኛ ድሏን ከትናንት በስቲያ ካስመዘገበች በኋላም ‹‹ቫሌንሲያ ከተማውንና ውድድሩን በጣም እወዳቸዋለሁ። ሁለተኛ ድሌን በስፔን በማስመዝገቤ እንዲሁም ሰዓቴን በማሻሻሌ እጅግ ደስተኛ ነኝ›› በማለት አስተያየቷን ሰጥታለች። ውድድሩን ሦስተኛ ሆና የፈፀመችው የ2015 የዓለም ቻምፒዮኗ ብርሃኔ ዲባባ ስትሆን የግል ሰዓቷን ያሻሻለችበትን 2:18:46 አስመዝግባለች። በውድድሩ ጫና ለመፍጠር የሞከረችው ኬንያዊት ቪቪያን ቼሩይት ደግሞ ከብርሃኔ በስድስት ሰከንዶች ዘግይታ አራተኛ ሆና ውድድሩን ፈፅማለች። ሌላኛዎቹ ኢትዮጵያዊያን ዘይነባ ይመር፣ ወርቅነሽ እዴሳ፣ አበባ ገብረመስቀልና ታደለች በቀለ ደግሞ አንዲት ኬንያዊትን ብቻ በጣልቃ ገብታባቸው ከአምስት እስከ ዘጠኝ ያለውን ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል። በወንዶች በኩልም ተካፋይ ከነበሩት አትሌቶች መካከል አራት የሚሆኑት ከዚህ ቀደም በማራቶን ከ2 ሰዓት ከ05 በታች መሮጥ የቻሉ መሆናቸው ከውድድሩ ቀደም ብሎ ከፍተኛ ፉክክር እንደሚካሄድበት ሲጠበቅ ነበር። ንፋሳማ በነበረው የአየር ሁኔታ አትሌቶቹ ከመነሻውም ተበታትነው ይሩጡ እንጂ ኢትዮጵያውያኑና ኬንያውያኑ አራት አትሌቶች ርዕስ በርዕስ ተከታጥለው ጠንካራ ፉክክር ሲያደርጉ ታይተዋል። የውድድሩን ግማሽ ወይም ሃያ አንድ ኪሎ ሜትሩን ለማገባደድ የፈጀባቸው ጊዜ 1:01:58 በመሆኑም የቦታው አዲስ ክብረወሰን እንደሚሰበር ፍንጭ የሰጠ ነበር። በመጨረሻም ክንዴ አጥናው መሪነቱን በማጠናከር አሸናፊ ሊሆን ችሏል። ርቀቱን በቀዳሚነት አጠናቆ ክሩን ለመበጠስ የፈጀበትም 2:03:51 የሆነ ሰዓት ነው። ከሩጫው በኋላም ‹‹አሁን ማራቶንን የማሸነፍ ጊዜው የእኔ መሆኑን አውቅ ነበር። በዝግጅት ወቅት አሸናፊ ለመሆን እሰራ ነበር፤ ይህም እውን ሆኗል›› ሲል ክንዴ አስተያየቱን ሰጥቷል። ቱርካዊው ካን ኪግን በ2:04:16 ሁለተኛ ሆኖ ሲገባ፤ ጉዬ አዶላና አበበ ደገፋ ደግሞ በሰከንዶች ልዩነት ሦስተኛና አራተኛ በመሆን ውድድሩን ፈጽመዋል። አሸናፊ ሞገስ፣ ፀጋዬ ጌታቸውና ልዑል ገብረሥላሴም እስከ አስር ባለው ደረጃ ተከታትለው መግብት የቻሉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ናቸው። ከማራቶን ውድድሩ ቀደም ብሎ እዚያው ቫሌንሲያ በተካሄደው የአስር ኪሎ ሜትር ውድድር ዩጋዳዊው አትሌት ጆሹአ ቺፕቴጌ የዓለም ክብረወሰን በማሻሻል ማሸነፉ ያልተጠበቀ ነበር። ከሁለት ወራት በፊት በዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በአስር ሺ ሜትር ፉክክር ሳይጠበቅ ኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻን አስከትሎ በመግባት ማሸነፍ የቻለው ቺፕቴጊ 26፡38 በሆነ ሰዓት የክብረወሰን ባለቤት ሆኗል። ይህ አትሌት በውድድር ዓመቱ በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ላይ አሸናፊ እንደነበር ይታወሳል። ከሳምንት በፊት የዓመቱ የዓለም ምርጥ አትሌቶች ሽልማት በሞናኮ ሲካሄድ ቺፕቴጌ ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች መካከል አንዱ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን አሁን ያሻሻለው ክብረወሰን ምናልባትም ከሳምንት በፊት ቢሆን የዓመቱ ምርጥ አትሌት ሽልማትን የማሸነፍ ከፍተኛ ዕድል ይኖረው ነበር። ቺፕቴጌ ያሻሻለው የዓለም የጎዳና ላይ አስር ኪሎ ሜትር ክብረወሰን እ.ኤ.አ 2010 ላይ በኬንያዊው ሊዮናርድ ፓትሪክ ኮመን የተያዘ ሲሆን ሰዓቱም 26፡44 ነበር። ሮዛ ደረጄ በቫሌንሲያ ማራቶን የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸናፊ ሆናለች፣ አዲስ ዘመን ኅዳር 23/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23492
[ { "passage": "ገንዘቤ ዲባባ በአዳራሽ ውስጥ ሩጫ ውድድር ለ 26 ዓመታት ተይዞ የቆየውን የአንድ ማይል የዓለም ክብረ ወሰን ሰበረች። ባሁኑ ወቅት 5 የዓለም ሬኮርድ ባለቤት ነች።ገንዘቤ ዲባባ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ አዲስ ያስመዘገበችው የዓለም ክብረ ወሰን 4 13 31 ሲሆን ላለፉት 26 ዓመታት ሳይደፈር ከቆየው ጊዜ ላይ አምስት ሴኮንዶች ግድም ላጭታለታለች።ገንዘቤ በተጨማሪ ሌላ ድል ከሁለት ቀናት በሁዋላ ተጎናጽፋለች። በስፔን ከተማ በሣባዴል ባዳራሽ ውስጥ የ 3 ሺህ ሜትር በታሪክ ፈጣኑን ጊዜ በማጻፍ አጠናቃለች።በሌላ የአትሌቲክስ ዜና፥ WADA ማለትም የዓለሙ የፀረ-ጉልበት ሰጪ መድሃኒት ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ፥ ኬንያን ከ 2016 ቱ የሪኦ ኦሊምፒክ ለማገድ መዘጋጀቱን አስታውቋል። ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ 40 የኬንያ አትሌቶች የጉልበት ሰጪ መድሃኒት ምርመራ አለማለፋቸው ተረጋግጧል። ", "passage_id": "f51995abbd331d23c6f4468f290cdc03" }, { "passage": "ከባድ በሆነውና ታላቅ ጽናትን በሚጠይቀው የአትሌቲክስ ዘርፍ ማራቶን ዓለም አቀፍ ተሳትፎዋን የጀመረችው ኢትዮጵያ፤ በበርካታ ገድሎች የአትሌቲክስ ታሪኳን አድምቃለች። ከኦሊምፒክ ቀጥሎ ታላቅ ስፍራ ባለው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናም የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ያስመዘገበችው በማራቶን ነው። ሃገሪቷ ካስመዘገበቻቸው 77 ሜዳሊያዎች መካከልም 10 የሚሆኑት በማራቶን የተገኙ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል ሁለቱ ወርቅ ሲሆኑ፤ አራት ብር እና አራት ነሃስ ናቸው። የኢትዮጵያ ተሳትፎ መነሻውን እአአ\nበ1983 በፊንላንዷ ሄልሲንኪ ካደረገው የዓለም ሻምፒዮና ሲጀመር በማራቶን የብር ሜዳሊያ ነው ሰንጠረዡ የተሟሸው። በወቅቱ ኢትዮጵያዊው አትሌት ከበደ ባልቻ በአውስትራሊያዊው ሮበርት ዴ ካስቴሌ ቢቀደምም ጀርመናዊውን ዋልዴማር ሴርፒኒስኪን በማስከተል የብር\nሜዳሊያ ተሸላሚ በመሆን ነበር ውድድሩን ያጠናቀቀው። ይህ ሜዳሊያም ኢትዮጵያን በሻምፒዮናው በብቸኝነት ያስጠራ ሆኖ ነው የተጠናቀቀው። ከዚያ\nበኋላ በተካሄዱት ዓለም ሻምፒዮናዎች በዚህ ርቀት ተሳትፎ እንጂ ውጤት ሳታስመዘግብ ነበር የቆየችው። ድሉ ወደ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች እስከተመለሰበት እአአ 2001 የኤድመንተን ሻምፒዮና ድረስም ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ ቆይቷል። ኤድመንተን ላይ የ23 ዓመቱ\nወጣት አትሌት ገዛኸኝ አበራ ባልተጠበቀ መልኩ ሌሎቹን አስከትሎ በመግባት ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያውን ለሃገሩ ማስመዝገብም ችሏል። በወቅቱ የአትሌት ገዛኸኝ አበራ\nየማራቶን እና የአትሌት ደራርቱ ቱሉ የ10ሺ\nሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎች ከሌሎቹ ጋር ተደምረው ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ሁለተኛ ከዓለም ደግሞ ስድስተኛ ደረጃን እንድትይዝ አድርገዋት ነበር። ገዛኸኝ በዚህ ውድድር የወንዶች ተሳትፎ እስካሁንም ያልተደገመ ድል ሲያስመዘግብ፤ በዓለም ሻምፒዮና ታሪክ ከገዛኸኝ ባነሰ እድሜ ማራቶንን ያሸነፈ አትሌት ባለመታየቱ ባለ ድርብ ክብር አትሌት ያደርገዋል። እአአ\nበ2009 በበርሊን በተካሄደው ሻምፒዮና የበላይነቱ በኬንያዊያን አትሌቶች ቢያዝም ኢትዮጵያዊው አትሌት ጸጋዬ ከበደ ግን የነሃስ ሜዳሊያውን በማጥለቅ ለሃገሩ የርቀቱን ሦስተኛ ሜዳሊያ አጥልቋል። ይህ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በማራቶን ሁለት ሜዳሊያ ያገኘችበት ሲሆን፤ በሻምፒዮናው ተሳትፎ ሴቶች የሜዳሊያ ሰንጠረዡን የተቀላቀሉበት የመጀመሪያው ዓለም ሻምፒዮናም ነው። በውድድሩ የቻይናና የጃፓን አትሌቶችን ተከትላ በመግባት የነሃስ ሜዳሊያውን ያጠለቀችው አትሌትም አሰለፈች መርጊያ ናት። በቀጣዩ የዴጉ\nየአትሌቲክስ ዓለም ሻምፒዮና ላይም ሌላኛው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በማራቶን የሜዳሊያ ሰንጠረዡን መቀላቀል ችሏል። አትሌቱ ሁለቱን ኬንያዊያን አትሌቶች ተከትሎ በመግባቱም ነበር የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነው። በ13ኛው\nየሞስኮ ዓለም ሻምፒዮና አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ እና ታደሰ ቶላ ዩጋንዳዊውን አትሌት ተከትለው የብርና የነሃስ ሜዳሊያዎችን አስመዝግበዋል። በሴቶች የታየው ውጤታማነት ግን ለሁለት ሻምፒዮናዎች ሳይደገም ነበር የቆየው። በቤጂንጉ ሻምፒዮና አትሌት የማነ ጸጋዬ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የብር ሜዳሊያውን ሲያገኝ፤ በሴቶች በኩል ሁለተኛው ሜዳሊያ የወርቅ ሆኖ ሊመዘገብ ችሏል። የጎዳና ላይ ሯጭ አትሌት ማሬ ዲባባ በሻምፒዮናው የኬንያ እና ባህሬን አትሌቶችን በማስከተልም ነው አሸናፊ ልትሆን የቻለችው። ከሁለት ዓመታት በፊት በለንደን በተካሄደው የዓለም ሻምፒዮናም በአትሌት ታምራት ቶላ የብር ሜዳሊያ ተመዝግቧል። ኢትዮጵያ በማራቶን ካስመዘገበቻቸው 10 ሜዳሊያዎች መካከል ስምንቱ ሜዳሊያዎች በወንዶች የተመዘገቡ ናቸው። በዓለም ዓቀፍ ደረጃም ባስመዘገቧቸው ሜዳሊያዎች 4ኛ ደረጃ\nላይ ሊቀመጡ ችለዋል። ከሦስት ወራት በኋላ በኳታሯ ዶሃ አስተናጋጅነት ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለ17ኛ\nጊዜ ይካሄዳል። በዚህ ሻምፒዮና ላይም ኢትዮጵያን አትሌቶች እንደተለመደው በርቀቱ የሚሳተፉ ሲሆን፤ ቡድኑን የሚወክሉት አትሌቶችም ታውቀዋል። በሻምፒዮናው ላይ በርካታ ሃገራትን ጨምሮ ማህበሩን የወከሉት የስደተኞችና በተለያዩ ምክንያቶች ለሃገራቸው የማይሮጡ በሺዎች የሚቆጠሩ አትሌቶችም ተሳታፊዎች ይሆናሉ። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በሁለቱም ጾታዎች የማራቶን ቡድኑን ከእነ ተጠባባቂዎቻቸው አስታውቋል። ምርጫውም አትሌቶቹ ባስመዘገቡት የተሻለ ሰዓት እንዲሁም በዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ዋና ዋና ውድድሮችና የወርቅ ደረጃ በተሰጣቸው ማራቶኖች ተሳትፏቸው የተመረጡ ናቸው። በውድድሮቹ ላይ እአአ ከሴፕቴምበር 2018- ኤፕሪል 2019 ድረስ ተወዳድረው ያስመዘገቡት የተሻለ ሰዓትም በሻምፒዮናው ሃገራቸውን እንዲወክሉ ያደርጋቸዋል። በወንዶች በኩል ስድስት አትሌቶች ቡድኑን ሲቀላቀሉ፤ በቅርቡ በተካሄደው የለንደን ማራቶን ተሳትፎው የኢትዮጵያን ክብረወሰን የሰበረው እና በዓለም ሦስተኛውን ፈጣን ሰዓት ያስመዘገበው አትሌት ሞስነት ገረመው በቅድሚያ የተመረጠ አትሌት ሊሆን ችሏል። ሞስነት ቀዳሚ ለመባል የቻለው ደግሞ ባስመዘገበው 2 ሰዓት ከ02 ደቂቃ\nከ55 ሰከንድ የሆነ ምርጥ ሰዓት ነው። ባለፈው ዓመት በቺካጎ ማራቶን ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው ሞስነት፤ እአአ በ2015ቱ\nየቤጂንግ ዓለም ሻምፒዮና 10ሺ ሜትር\nሃገሩን እንደወከለ የሚታወስ ነው። በለንደኑ ማራቶን ከሞስነት ጋር በአንድ ደቂቃ ልዩነት የግሉን ፈጣን ሰዓት ማስመዘግብ የቻለው አትሌት ሙሌ ዋሲሁን ለቡድኑ በሁለተኛነት ተመርጧል። አትሌቱ ያለው ሰዓት 2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ\nከ16 ሰከንድ ሲሆን፤ እአአ በ2016 የካርዲፍ ግማሽ\nማራቶን ሻምፒዮና፤ ስምንተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው። ሌላኛው አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳም ባስመዘገበው ሰዓት ቡድኑን የተቀላቀለ ሦስተኛው አትሌት ነው። እአአ በ2013ቱ\nየሞስኮ ዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ለሃገሩ ያስመዘገበው አትሌቱ፤ ባለፈው ዓመት በተካሄደው የኒውዮርክ ማራቶን የገባበት 2 ሰዓት ከ05 ደቂቃ\nከ59 ሰከንድ የሆነ ሰዓት ተመራጭ አድርጎታል። በማራቶን ዝነኛ ከሆኑ የዓለም አትሌቶች መካከል ተጠቃሽ የሆነው ሌሊሳ፤ ከኒውዮርክ ጎዳናዎች ባሻገር በቦስተን ማራቶንም ተደጋጋሚ ድሎችን አጣጥሟል። ዘንድሮ ባደረገው አራተኛ ተሳትፎውም ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው አትሌቱ። በሴቶች በኩልም በተመሳሳይ ሦስት አትሌቶች የተመረጡ ሲሆን፤ አትሌት ሩቲ አጋ ባላት ሰዓት ቡድኑን ትመራለች። አትሌቷ ቀዳሚ ምርጫ ልትሆን የቻለችው ባለፈው ዓመት በተካሄደውና የወርቅ ደረጃ ባለው የበርሊን ማራቶን ባስመዘገበችው 2 ሰዓት ከ18ደቂቃ\nከ34 ሰከንድ የሆነ ምርጥ ሰዓቷ ነው። አትሌቷ ከወራት በፊት በተካሄደው የቶኪዮ ማራቶን 2:20:40 በሆነ ሰዓት አሸናፊ ነበረች። በዚህ ዓመቱ የዱባይ ማራቶን 2 ሰዓት 17ደቂቃ ከ41 ሰከንድ የገባችው አትሌት ወርቅነሽ ደገፉም በቡድኑ የተካተተች ሁለተኛዋ አትሌት ናት።\nበማራቶን ውድድሮች የተሻለ ውጤት ያላት አትሌቷ፤ ከዱባይ በኋላ በተካሄደው የቦስተን ማራቶን አሸንፋለች። በባለፈው ዓመቱ የዱባይ ማራቶን 2 ሰዓት ከ19ደቂቃ\nከ17ሰከንድ ያስመዘገበችው ሌላኛዋ አትሌት ሮዛ ደረጀም በሻምፒዮናው ሃገሯን እንደምትወክል አረጋግጣለች። በወንዶች በኩል በተጠባባቂነት ሦስት አትሌቶች የተያዙ ሲሆን፤ በቅርቡ በለንደኑ ማራቶን ተሳታፊ የነበረው ሹራ ኪጣታ ባለው ሰዓት ቀዳሚው ተጠባባቂ ሆኗል። ሹራ በዚህ ማራቶን 2ሰዓት ከ05ደቂቃ\nከ01ሰከንድ የሆነ ሰዓት አስመዝግቧል። በተመሳሳይ በዚህ ዓመት በተካሄደው የቶኪዮ ማራቶን ተሳትፎው 2ሰዓት ከ04 ደቂቃ\nከ48ሰከንድ በመግባት ያሸነፈው አትሌት ብርሃኑ ለገሰ ሁለተኛው ተጠባባቂ ነው። ባለፈው ዓመት የዱባይ ማራቶንን 2ሰዓት ከ04ደቂቃ\nከ06 ሰከንድ የሮጠውና በለንደኑ የዓለም ሻምፒዮና በማራቶን ብቸኛውን ሜዳሊያ ያስመዘገበው አትሌት ታምራት ቶላም በተጠባባቂነት ከተያዙ አትሌቶች መካከል ይገኛል። በቶኪዮ ማራቶን በሰከንዶች ተበላልጠው ውድድራቸውን የፈጸሙት አትሌት ሹሬ ደምሴ እና ሄለን ቶላ ደግሞ በሴቶች በኩል በተጠባባቂነት የተያዙ አትሌቶች ናቸው። ከሄልሲንኪ የጀመረው\nየኢትዮጵያ የማራቶን ድል እስከ\nዶሃ እንዲዘልቅም ዝግጅቱ\nከወዲሁ ተጀምሯል። በውድድሩ\nህግ መሰረት ለሻምፒዮናው\nየተመረጠ አትሌት ለሦስት\nወራት የማገገሚያ ጊዜ የግድ\nያስፈልገዋል። በዚህም መሰረት\nአሁን አትሌቶቹ ከውድድር\nርቀው በአሰልጣኞቻቸው ልምምድ\nበማድረግ ላይ ይገኛሉ።\nበመጪው ሐምሌ ወር በሻምፒዮናው ተሳታፊ የሚሆኑ\nአትሌቶችን ለመምረጥ በኔዘርላንድ\nሄንግሎ ከሚካሄደው የሟሟያ\nውድድር በኋላም ብሄራዊ\nቡድኑ ወደ ካምፕ\nገብቶ ልምምዱን እንደሚጀምር\nየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን\nመረጃ ያመላክታል።አዲስ ዘመን ሀምሌ 8/2011 ", "passage_id": "e1b7442d800b9ee7d781bdfcb6823f6e" }, { "passage": "ታምራት ቶላ በዓርቡ የዱባይ ማራቶን የኮርሱን ሪኮርድ በመስበር ጭምር አሸንፉዋል። የሴቶቹን ወርቅነሽ ደገፋ መርታለች።አዳጊው ኮከብ አትሌት ሰሎሞን ባረጋ እና በየኑ ደገፉ። በእሁዱ የኢጣልያ አገር አቋራጭ ውድድር የበላይነቱን ወስደዋል።በስፔኑ አገር አቋራጭም ድሉ የኢትዮጵያ ሆኗል። ሰንበሬ ተፈሪ በአንደኝነት አጠናቃለች። የሃገር ውስጥና የውጭ ሀገር እግር ኳስ ዜናዎችም ይዘናል፡፡ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። ", "passage_id": "22d3d1bd012aa3ab98c5037c208e7cbd" }, { "passage": " ኬንያዊው የማራቶን የዓለም ክብረወሰን ባለቤት ኢሉድ ኪፕቾጌ በናይኪ የተያዘውን ከሁለት ሰዓት በታች የመግባት ሙከራ አሳካ። ትናንት በኦስትሪያዋ ቬና በተካሄደው ሙከራ ላይ ኢሉድ ኪፕቾጌ 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት በመግባት ዓላማውን ማሳካት ችሏል። አትሌቱ በታሪክ 42ኪሎ ሜትርን ከሁለት ሰዓት በታች የገባ የመጀመሪያው ሰው ይሁን እንጂ ሰዓቱ በዓለም ክብረወሰንነት አይመዘገብለትም። የሰው ልጅ አቅም ወሰን የሌለው መሆኑን ለማሳየት በታዋቂው የስፖርት ትጥቅ አምራች ናይኪ የተያዘው ይህ ፕሮጀክት በአትሌቲክስ ስፖርት ረጅሙን ርቀት ከተለመደው ሁለት ሰዓት በታች ለመግባት የሚያስችል ሙከራ ነው። ለዚህም የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ ኪፕቾጌ የተመረጠ ሲሆን፤ ትጥቅ አምራቹ በሚያደርገው በቴክኖሎጂ የታገዘ ድጋፍ 1ሰዓት ከ59 ደቂቃ ለመግባት ነበር የታቀደው። ለዚህ ሙከራ ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ያላትና ሰዓቱን ለማሟላት የሚያስችል የቦታ አቀማመጥ ያላት ቬና ስትመረጥ፤ ከ41 በላይ የሆኑ አሯሯጮችም ተዘጋጅተው ነበር። ትናትን ጠዋት በተካሄደው ሩጫም አትሌቱ የርቀቱን ግማሽ የሸፈነበት ሰዓት አጠራጣሪ ይሁን እንጂ በአሯሯጮቹ ብርታት 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት በመፈጸም ግቡን ሊያሳካ ችሏል። ከሩጫው በኋላም «አሯሯጮቹን ላመሰግናቸው እወዳለሁ፤ ይህንን ሙከራ ተቀብለው አብረውኝ በመሮጣቸው ታሪክ ለማስመዝገብ ችለናል። ይህ በርካቶችን የሚያነሳሳ እና የሰው ልጅ አቅም የሚገደብ አለመሆኑንም ያሳያል። በጣም ደስ ብሎኛል ልጆቼ እና ባለቤቴም ሩጫዬን በመመልከታቸው ተደስቻለሁ» ማለቱን ኢንዲፔንደንት በድረገጹ አስነብቧል። ሙከራው በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ዕውቅና የሌለው መሆኑን ተከትሎ በዓለም ክብረወሰንነት አይመዘገብም። እ.አ.አ በ2018 የበርሊንን ማራቶን የገባበት 2፡01.39 የሆነ ሰዓት የዓለም ፈጣን ሰዓት ሲሆን፤ ከሁለት ዓመት በፊት አትሌቱ በጣሊያኗ ሞንዛ ከተማ ባደረገው ሙከራ በ26ሰከንዶች ዓላማውን አለመሳካቱ ይታወሳል።አዲስ ዘመን ጥቅምት 2/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "169d6bee9edecbfefa269a65fb02c866" }, { "passage": "ብርሃን\nፈይሳ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ ውድድሮች ላይ በሚያስመዘግቧቸው ድሎች ይታወቃሉ። ታላቅ ክብርን እንዲቀዳጁ ምክንያት የሆናቸው ግን በየጊዜው በሚሰባብሯቸው የዓለም ክብረወሰኖች ነው። ይህ ደግሞ ለረጅም ዓመታት ያልተደፈሩ ክብረወሰኖችን ከመስበር ባሻገርም ለረጅም ዓመታት ከእጃቸው ሳይወጣ የሚቆይም ነው። እንደተለመደው ሁሉ ባለፉት ሁለት ሳምንታትም ሁለት የዓለም ክብረወሰኖችን በማስመዝገባቸው አድናቆት እየተቸራቸው ይገኛል። አትሌት ሳሙኤል ተፈራ እና አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ የግላቸው ያደረጓቸው አዳዲስ ክብሮችም፤ ኢትዮጵያውያ በዓለም ደረጃ ያስመዘገበችውን የክብረወሰን ቁጥር ወደ አስር ያሳደገ ሆኗል። ይሄ\nሰዓትን አሻሽሎ መግባት በርቀቱ የቁጥር አንድነት ማዕረግ ከማስገኘቱም ባለፈ፤ ለአትሌቱ የትልልቅ ውድድሮችን በር ይከፍትለታል፤ የስፖንሰሮችን ፍላጎት ይስባል። በዛሬው እትምም በወንድ አትሌቶች የተሰበሩትን ክብረወሰኖች እንመለከታለን። ኢትዮጵያ በታወቀ ችበት የረጅም ርቀት አትሌቲክስ ዘርፍ ፈጣን ሰዓቶች የተመዘገቡት በአንድ አትሌት ነው። ይህ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሲሆን፤ በአንድ ዓመት ልዩነት በ5ሺ እና 10ሺ ሜትሮችን ክብር የግሉ ማድረግ ችሏል።እ.አ.አ በ2004 ሄንግሎ ላይ በተካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ በ5ሺ ሜትር የተሳተፈው አትሌቱ የርቀቱን የመጨረሻ መስመር የረገጠው በ12ደቂቃ ከ37ሰከንድ ከ35 ማይክሮ ሰከንድ ነው። በቀጣዩ ዓመት በከባድ ሁኔታ ውስጥ የነበረው አትሌቱ የውድድር ዓመት አጀማመሩ ጥሩ ባይሆንም አቋሙን እያሻሻለ በመሄድ በሄልሲንኪው የዓለም ሻምፒዮና በ5ሺ እና 10ሺ ሜትሮች ሻምፒዮን መሆን ችሏል። በቀናት ልዩነት ብራሰልስ ላይ በተካሄደው ሌላ ውድድርም በ10ሺ ሜትር ተሳታፊ ሆኖ ነበር። ክብረወሰን በሰበረበት በዚህ ውድድር ላይም ርቀቱን ለማጠናቀቅ በአጠቃላይ 26 ደቂቃ ከ17 ሰከንድ ከ53 ማይክሮ ሰከንድ ፈጅቶበታል። 20ሺ\nሜትር የሚሸፍነው ውድድር ክብረወሰን የተያዘውም በኢትዮጵያዊው አትሌት ሲሆን፤ ይኸውም በሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ነው። ወቅቱም እ.አ.አ በ2007 ኦስትራቫ ላይ በተካሄደው ውድድር ሲሆን፤ ርቀቱን የሮጠውም 56 ደቂቃ ከ25ሰከንድ ከ98 ማይክሮ ሰከንድ ነበር። በዚያው ዓመት በዚያው ከተማ በአንድ ሰዓት የቻሉትን ያህል ርቀት ለመሸፈን በሚካሄደው ውድድር ላይም በተመሳሳይ ክብረወሰኑ የተያዘው በአንጋፋው አትሌት ነው። ኃይሌ ክብረወሰኑን በስሙ ያስመዘገበውም 21ሺ285 ሜትር በመሮጡ ነው። ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በሚያዘጋጀው የቤት ውስጥ ውድድሮችም በተመሳሳይ በርካታ ክብረወሰኖች በኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተሰብረዋል። በመካከለኛ ርቀት ከሁለት አሥርት ዓመታት በፊት የቆየው ክብረወሰን ከቀናት በፊት በኢትዮጵያዊው ወጣት አትሌት መሻሻሉም የሚታወስ ነው። የ20ዓመቱ ሳሙኤል ተፈራ በበርሚንግሃም የተካሄደውን የ1ሺ500 ሜትር ውድድር ለማጠናቀቅ 3ደቂቃ ከ31ሰከንድ ከ04 ማይክሮ ሰከንድ የፈጀበት ሲሆን፤ ሰዓቱን በ14ሰከንዶች ነው ያሻሻለው። ከሳምንት በፊት የተሰበረው ሌላኛው ክብረወሰን ደግሞ በአንድ ማይል ርቀት ሲሆን፤ ቁመተ መለሎው ዮሚፍ ቀጄልቻ ደግሞ የክብሩ ባለቤት ነው። ዮሚፍ በቦስተን በተካሄደው ውድድር ላይ በሞሮኳዊው አትሌት ሂቻም ኤል ግሩዝ ለሁለት አሥርት ዓመታት የቆየውን ክብረወሰን ከእጁ ለማስገባትም 3ደቂቃ ከ47ሰከንድ 01ማይክሮ ሰከንድ ሮጧል። በ5ሺ ሜትር የሪከርድ ባለቤት የሆነው ቀነኒሳ በቤት ውስጥ ውድድር የርቀቱ ክብር የግሉ ነው። አትሌቱ የክብረወሰን ባለቤት የሆነው በበርሚንግሃም እ.አ.አ በ2004 በተካሄደው ውድድር ሲሆን፤ የገባበት ሰዓትም 12ደቂቃ ከ49ሰከንድ ከ60 ማይክሮ ሰከንድ ነበር። ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ውጪ በሚዘጋጁና በማህበሩ ደረጃ በተሰጣቸው ውድድሮች ላይም ኢትዮጵያውያን የክብረወሰን ባለቤት ናቸው። እ.አ.አ በ2011 ድሪባ መርጋ የ8ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ የተሳተፈ ሲሆን፤ 21ደቂቃ ከ51ሰከንድ ደግሞ ርቀቱን ለማጠናቀቅ የፈጀበት ሰዓት ነው። በ10ማይል የጎዳና ላይ ሩጫ ክብረወሰን በአንጋፋው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ እ.አ.አ በ2005 ሲያዝ ለረጅም ዓመታት ሊበገሩ ካልቻሉት መካከል የሚጠቀስም ነው። ኃይሌ የክብረወሰን ባለቤት የሆነውም ባስመዘገበው 44ደቂቃ ከ24ሰከንድ በሆነ ሰዓት ነው። በቤት ውስጥ የ2ሺ ሜትር ውድድርም በተመሳሳይ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 4ደቂቃ ከ49ሰከንድ ከ99ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት የተያዘ ነው።አዲስ\nዘመን መጋቢት 2/2011በብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "0210df94ad750aa8fee0ec833010b739" } ]
9c83e168717bc72026c3341fae950960
48933cfd926f37a6b1251aab5639163c
የኢቨስትመንት ህጉ መሻሻል ለቴክኖሎጂ ሽግግርና የሥራ እድል ፈጠራ እንደሚያግዝ ተገለጸ
በኃይሉ አበራአዲስ አበባ:- የኢንቨስትመንት ህጉ መሻሻል የቴክኖሎጂ ሽግግሩን በማረጋገጥ፣ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በማሻሻል፣ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት እና ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር በኩል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሰሞኑ ከእስራኤል፣ ከእንግሊዝ እና ከአውስትራሊያ ከመጡ ባለሀብቶች ጋር በተሻሻለው የኢንቨስትመንት ህግና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በአዲስ አበባ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሂዷል።በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ መኮንን ኃይሉ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ መንግሥት የኢንቨስትመንት ህጉን በማሻሻል፣ የግሉን ዘርፍ ሚና በማጎልበት እንዲሁም ኢትዮጵያ ከመቼውም በላይ ለቢዝነስ የተሻለችና ምቹ እንድትሆን ከማድረግ አንጻር በትኩረት እየተሰራ ነው። ይህም የውጭ ባለሀብቶችን ተሳትፎ በማሳደግ ኢንቨስትመንቱን እያሳደገው ይገኛል።በሀገራችን በተካሄደው የፖለቲካ ሪፎርም በሌላኛው ጎኑ የኢኮኖሚ መሻሻሎች ማምጣቱን የገለጹት አቶ መኮንን፤ ኢትዮጵያ ያሻሻለችው የኢንቨስትመንት ሕግ በምስራቅ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ደረጃ በኢትዮጵያ ያለው መደላደል ምቹ መሆኑን ግንዛቤ መወሰዱን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ እንድትሆን ከማድረግ አንጻር ባለፉት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ አስተባባሪነት እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ተሳትፎ ተቋማቶችን ባካተተ መልኩ የንግድና ኢንዱስትሪ፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የባንክና ሌሎች መሰል ነገሮች ጋር በተያያዘ ኢንቨስትመንቱን የማቅለል ስራዎች እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ መኮንንን እንደሚሉት፤ አንክታድ በሚባል ዓለም አቀፍ ሪፖርት በቅርቡ ባወጣው መረጃ ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ከምስራቅ አፍሪካ ግንባር ቀደም ላይ ትገኛለች፤ በአፍሪካ ደረጃ ደግሞ ከግብጽ፣ ከደቡብ አፍሪካ፣ ኮንጎና ሞሮኮ በመቀጠል በአምስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በመሆኑም በሀገራችን የውጭ እና የሀገር ውስጥ ተሳትፎ የሚያሳድግ እና የግል ዘርፉን ሰፋ ባለ መልኩ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችል የኢንቨስትመንት ሕግ ተሻሽሎ መቅረቡ ሀገራችን የበለጠ የወጭ ባለሀብቶች ትኩረት እንዲኖራት ያስችላታል። ይህ ደግሞ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ እድል ከመፍጠር አንጻር የጎላ እና የላቀ ሚና ይኖረዋል። እንዲሁም የውጭ ምንዛሪ ግኝት እና የቴክኖሎጂ ሽግግሩንም የተሻለ ያደርገዋል፤ ነው ያሉት።የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በበዙ ቁጥር ኅብ ረተሰቡ በሚያገኘው አቅርቦት ከትምህርት ቤት፣ ከሆስፒታሎችና መሰል የመሠረተ ልማት እና የማህበራዊ ተቋማት አገልግሎት እያደጉ የሚመጡ በመሆኑ ለዜጎች የሥራ እድል ፈጠራ ባሻገር የማህበራዊ ተቋማት አገልግሎትን በማሳደግም በቀጥታ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉም ነው አቶ መኮንን የገለጹት።በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ተሳታፊ የነበሩት አቶ አሰፋ፣ መንገሻ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በፀሐይ ኃይል ውሃ የሚያሞቁ መሳሪያዎችን የሚያመርት ፋብሪካ በሰንዳፋ የኢንዱስትሪ ዞን ውስጥ ያቋቋሙ ባለሃብት ናቸው። በእስራኤል ሀገር ከ30 ዓመት በላይ መኖራቸውን የገለጹት አቶ አሰፋ እንደሚሉት፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን ኢንቨስትመንት ከማሻሻል አንጻር ጥሩ እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን ነገር ግን ከዋና ኮሚሽኑ ከወጣ በኋላ ያለው የቢሮክራሲ ሁኔታ በጣም መሻሻል ይኖርበታል።አሁን ያለው የኢንቨስትመንት ህግ መሻሻልን ተከትሎ የኢንቨስትመንት የአቀባበል ሁኔታውን ማፋጠን ከተቻለ፣ እስራኤል አነስተኛ አገር ብትሆንም የቴክኖሎጂ ባህር እንደመሆኗ በእርሻ፣ በሶላር እና ሌሎችም በርካታ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ከእስራኤል ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ እንደሚችሉ ነው አቶ አሰፋ የተናገሩት። በፀሀይ ኃይል ውሃ የሚያሞቁ መሳሪያ ማምረቻው ወደ ሀገራችን ቢገባ ያለውን ጠቀሜታና አዋጭነት በማሰብ እና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት በሚል ቴክኖሎጂውን ማቋቋማቸውን የገለጹት አቶ አሰፋ፤ ፋብሪካውን ካቋቋሙ ስድስት ዓመት እንደሆነውና ምርት ማምረት ከጀመረ አራት ዓመት እንደሆነው ተናግረዋል። ከብዙ ድካምና ውጣውረድ በኋላም በግል መኖሪያ ቤቶች በፔንሲዮኖች፣ በአፓርትመንቶች፣ በሆቴሎች እና ጤናጣቢያ ላይ ሁሉ መግጠም መጀመራቸውን ገልጸዋል። አቶ አሰፋ፣ በእስራኤል ሀገር ሲኖሩ በነበረበት ቅቡጽ በሚባል ኩሚዩናል በሚኖርበት አካባቢ የእርሻ ሂደቱን ታዝበዋል። በሦስት ወር እና በአራት ወር ውስጥ የተለያየየምርት አይነት ይመረትበታል ብለዋል። በሦስት ወር እና በአራት ወር ውስጥ መሬቱ በተለያየ የምርት አይነት ይሸፈናል። ብዙ ሄክታር መሬት በበቆሎ ተሸፍኖ ይታያል፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ደግሞ ያንን የዚያ ምርት ተሰብስቦ መሬቱን አለስልሰው በዚያ በቆላ መሬት ላይ የተንጣለለ የስንዴ ማሳ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሲያሰሩ ይታያል፤ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ደግሞ አትክልቶች ሲሰራበት መመልከታቸውን ገልጸዋል። ይሄንን ቴክኖሎጂ በሀገራችን ተግባራዊ በማድረግ ኢትዮጵያን በይበልጥ የአፍሪካ የዳቦ ቅርጫት ማድረግ ይቻላል፤ የስንዴ ቋት መሆን እንችላለን። ቴክኖሎጂውን ደግሞ ለመቀበል እና ወደ ፊት ለማራመድ በሀገራችን በእርሻ ኢንጂነሪንግ የተማሩ ሰዎች በኩል ቴክኖሎጂውን በማስፋፋት ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታውን በማገናዘብ ከራሳችን አልፈን ለሌላው ሀገር ማቅረብ የሚቻልበትን ሰፊ እድል አለ ብለዋል። በሀገራችን ባሌና አርሲ የስንዴ ሜዳ መሆናቸው እንደሚታወቀው ሁሉ በወሎ እና አፋር ድንበር ላይ ከፍተኛ የስንዴ ምርት ማምረት ይቻላል። በሱማሌ ክልል ገናሌና ሸበሌ ወንዞች አሉ ሜዳው የሰጠ ነው ሰላም እና ደህንነት እስካለ ድረስ ከራሳችን አልፈን ምርቱን ሽጠን ለሌላም ሀገር መቀለብ የሚያስችል አቅም አለ። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ አይደለችም የሚለውን የውጪ ኢንቨስተሮች እይታ ለመቀየር ኢትዮጵያውያን የሀገራችንን ጥቅም በሚጠብቅ ሁኔታ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በግልጽ በመወያየት እና ግብረመልስ መስጠት ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል። የምርት አይነት ይመረትበታል ብለዋል። በሦስት ወር እና በአራት ወር ውስጥ መሬቱ በተለያየ የምርት አይነት ይሸፈናል። ብዙ ሄክታር መሬት በበቆሎ ተሸፍኖ ይታያል፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ደግሞ ያንን የዚያ ምርት ተሰብስቦ መሬቱን አለስልሰው በዚያ በቆላ መሬት ላይ የተንጣለለ የስንዴ ማሳ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሲያሰሩ ይታያል፤ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ደግሞ አትክልቶች ሲሰራበት መመልከታቸውን ገልጸዋል። ይሄንን ቴክኖሎጂ በሀገራችን ተግባራዊ በማድረግ ኢትዮጵያን በይበልጥ የአፍሪካ የዳቦ ቅርጫት ማድረግ ይቻላል፤ የስንዴ ቋት መሆን እንችላለን። ቴክኖሎጂውን ደግሞ ለመቀበል እና ወደ ፊት ለማራመድ በሀገራችን በእርሻ ኢንጂነሪንግ የተማሩ ሰዎች በኩል ቴክኖሎጂውን በማስፋፋት ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታውን በማገናዘብ ከራሳችን አልፈን ለሌላው ሀገር ማቅረብ የሚቻልበትን ሰፊ እድል አለ ብለዋል። በሀገራችን ባሌና አርሲ የስንዴ ሜዳ መሆናቸው እንደሚታወቀው ሁሉ በወሎ እና አፋር ድንበር ላይ ከፍተኛ የስንዴ ምርት ማምረት ይቻላል። በሱማሌ ክልል ገናሌና ሸበሌ ወንዞች አሉ ሜዳው የሰጠ ነው ሰላም እና ደህንነት እስካለ ድረስ ከራሳችን አልፈን ምርቱን ሽጠን ለሌላም ሀገር መቀለብ የሚያስችል አቅም አለ። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ አይደለችም የሚለውን የውጪ ኢንቨስተሮች እይታ ለመቀየር ኢትዮጵያውያን የሀገራችንን ጥቅም በሚጠብቅ ሁኔታ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በግልጽ በመወያየት እና ግብረመልስ መስጠት ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37781
[ { "passage": "ራስወርቅ ሙሉጌታአዲስ አበባ፦ በአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ መመስረት የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግና ግሽበትን ለመቀነስ ብሎም የእውቀት ሽግግር እንዲስፋፋ ለማድረግ እንደሚረዳ ተገለፀ። የአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ ትስስር በጥንቃቄ ከተመራ እያንዳንዱን የአፍሪካ ሀገር ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተጠቆመ። በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ዶክተር ደመላሽ ሀብቴ በጋራ የነፃ ገበያ ዙሪያ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በአፍሪካ አገራት መካከል የተቀናጀ የኢኮኖሚ ግንኙነት ባለመኖሩ አህጉሪቱ ከሰማንያ በመቶ በላይ የንግድ እንቅስቃሴዎች እያደረገች ያለችው ከአውሮፓ፣አሜሪካና እስያ አገራት ላይ ጥገኛ በመሆን ነው። በዚህም የተነሳ አህጉሪቱ ደካማ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ፣ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት የሚከሰትባትና ዝቅተኛ የእውቀት ሽግግር የሚስተዋልባት ሆና ቆይታለች። ከዚህ ቀደምም የአፍሪካ አገራት እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ትስስር ለማሳደግ የተሠሩ ጅምሮች ቢኖሩም ውጤታማ ባለመሆናቸው እስከ አሁን እርስ በእርስ ያላቸው ግንኙነት ከሃያ በመቶ የዘለለ አልነበረም ያሉት ዶክተር ደመላሽ፤ በተመሳሳይ ደረጃ የሚገኙ የኢንዱስትሪ ግብአቶችንም ሆነ እንደ ነዳጅ ያሉ ያለቀላቸውን ምርቶች አፍሪካ አገራት ውስጥ በስፋት እየተመረቱ ቢሆንም ሌሎች ተጠቃሚ ጎረቤት አገራት የሚያስገቡት ካደጉት አገራት ነው ብለዋል። በአህጉሪቱ የተጠናከረ የንግድ ልውውጡና የዳበረ የነፃ ገበያ ተፈጥሮ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው የተቀላጠፈ እንዲሆንና በሚጠበቀው ደረጃ እንዲያድግ የአፍሪካ አገራት የንግድ ልውውጥ በጋራ ነፃ ገበያ ሊጠናከርና ሊስፋፋ ይገባዋል ብለዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ መመስረትና ወደተግባር መግባት አፍሪካ እንደ አህጉር ከሌላው ዓለም ጋር ለሚኖራት የንግድና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶች በር የሚከፍት እንደሚሆንም አመልክተዋል። ነፃ ገበያው በአሁኑ ወቅት በስፋት የሚታየውን ወደመካከለኛው ምሥራቅና ሌሎች አገራት የሚደረገውን የሰው ኃይል ፍልሰት ወደአፍሪካ እንዲሆን ያግዛል ያሉት ዶክተር ደመላሽ፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የእውቀት ሽግግሩም በየደረጃው የተቀላጠፈ እንዲሆን ይረዳል፤ በአገራት መካከል የሚኖረውም የዲፕሎማሲ ግንኙነት የተጠናከረ እንዲሆን ያግዛል ብለዋል። የአፍሪካ አገራት የጋራ የነፃ ገበያ ከመሰረቱ ከፈለጉ በዶላር ወይንም በራሳቸው በሀገራቱ የመገበያያ ገንዘብ እንዲሁም እቃ በእቃ የመገበያየት ዕድሉ ስለሚኖራቸው የውጭ ምንዛሬ እጥረትን እንደሚቀንስ ጠቁመው፤ ይህም ሆኖ የመንግሥት ታክስ ሊቀንስ ይችላል እንዲሁም በአገራቱ መካከል የተመጣጠነ ዕድገት ባለመኖሩ የሚፈጠር ጫና ሊኖር እንደሚችል አመልክተዋል።የአፍሪካ የጋራ የነፃ\nገበያ ትስስር በጥንቃቄ\nእየተቆጣጠሩ መሥራት፣ ትልልቅ\nተቋማትን መገንባትና ጥራት\nያላቸውን ምርቶች በማምረት\nለጠንካራ ውድድር መዘጋጀት\nከተቻለ እያንዳንዱ የአፍሪካ\nአገር ተጠቃሚ ይሆናል\nሲሉም ዶክተር ደመላሽ\nተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2013 ", "passage_id": "28261b71f98d88d96d6d45cfc834543c" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ ሃምሌ 24/2005 (ዋኢማ) – አራተኛው የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡ የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን እንዳለውም የመድረኩ ዓላማ በኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢቨስትመንት ላይ በመወያየት ከዚያ የሚገኙ አዳዲስ ሃሳቦችን ለፖሊሲ አፍላቂዎች ግብዓት እንዲሆን ማድረግ ነው ።ኢትዮጵያን እንደ አውሮፓውያኑ የቀን አቆጣጠር በ2025 መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገራት ተርታ ለመሰለፍ በርካታ ስራዎችን እያከናወነች መሆኗ ይታወቃል።በዛሬው መድረክ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዲኤታው  አቶ ሲሳይ ገመቹ  እንዳመለከቱትም ፥ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ የኢንዱስትሪ መስኩን ማስፋፋትና የኢኮኖሚ መሪነቱን ከግብርናው ዘርፍ እንዲረከብ ማድረግ ዋናው ትኩረት ሊሆን ይግባል ።ኢትዮጵያ በርካታ ኢንዱስትሪዎችን ለመትከልና ኢኮኖሚያዊ እድገቷን ለማፋጠን ወደ ትግበራ የገባች ሲሆን ፥ አሁን ባለው ሁኔታም ዕቅዱን ማሳካት እንደሚቻል ነው ሚኒስትር ዲኤታው የተናገሩት።ይሁን እንጅ የአቅም ግንባታ ፣ የኢንዱሰትሪው ዘርፍን  ጠቀሜታ ለባለሃብቱ የማስተዋወቅ እና የመሰረት ልማት አቅርቦት  በበቂ ሁኔታ አለመከናወን ለዘርፉ ማነቆዎች መሆናቸውን ነው ያነሱት።ከዚህ አኳያም በዘርፉ የሚስተዋሉትን ችግሮች ለመቅረፍ በርካታ ስራዎች እየሰተሩ ስለመሆኑም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ዋና ስራ አስከያጅ አቶ ፍጹም አረጋ በበኩላቸው ፥ ካሁን ቀደም ባሉት አዋጆች ላይ ማሻሻያዎችን ለማድረግ መታቀዱን ነው የሚገልፁት።እነዚህ በአዱስትሪው መስክ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሃገራት በመነሳት የተዘጋጁት መመሪያዎች የሚፀድቁ ከሆነም ፥  የውጭ ቀጥታ አንቨስትመንትን ከመሳብ አንፃር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸውም ነው አቶ ፍፁም የሚናገሩት ሲል ፋና ዘግቧል።በጃፓን የፖሊሲ አማካሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ኪንቼ ኦህኖ ደግሞ ፥ ኢትዮጵያ ወደ አንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋጋር የሚያበቃ እምቅ አቅም አላት ይላሉ።ለውጭና ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች የሚመች ፖሊሲ ፣ በቀላል ዋጋ የሚገኝ የሰው ሃይልና ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ መስክ ላይ እየሰለጠነ ያለ የተማረ የሰው ሃይል ዋናዎቹ ሲሆኑ ፥ በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ ሁሉንም ማሟላት እንደምትችል ገልጸዋል።", "passage_id": "f940c0f4aea73b3666c3e6e15ef4ea77" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችንና ምሩቃንን በዘመናዊ የሶፍትዌር መተግበሪያ አሰልጥኖ ወደ ቴክኖሎጂ ለማስገባት ያቀደ ሃሳብ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ፕሮፈሰር አፈወርቅ ካሱ፥ ከሃገርኛ ድርጅት ስራ አስኪያጅ ቢያግ ሚን ጋር በቀረበው ሃሳብ ላይ ተወያይተዋል።የቀረበው ሃሳብ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን እና ስራ ፈላጊ ምሩቃንን አስፈላጊ የኮምፒውተር ቋንቋዎችን በማሰልጠን ለማብቃት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ፕሮፈሰር አፈወርቅ ካሱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጅ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።በኢትዮጵያ እንደ ጃቫ ባሉ የኮምፒውተር ቋንቋ ዘርፍ በቂ የሰለጠኑ ባለሙያዎች አለመኖራቸውን ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ተማሪዎችንና ምሩቃንን በማብቃት በኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪው ውስጥ እንዲሰሩ ለማዘጋጀት እቅድ እንዳላቸውም ነው የተናገሩት።ፕሮፌሰር አፈወርቅ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለእቅዱ ተግባራዊነት አብሮ እንደሚሰራ ጠቅሰዋል።ሃገርኛ በኮሪያ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ በነበሩ ኢትዮጵያውያን የዛሬ 10 ዓመት የተሰራ አማርኛ ለመፃፍ የሚያስችል የሞባይል መተግበሪያ ስያሜ መሆኑን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።", "passage_id": "824479db1fd4c53e8d2186e4b9448fd6" }, { "passage": "በኢትዮጵያ የሥራ ፈጣሪዎች ማኅበር መስራችና ፕሬዝዳንት የሆነችው ሳሚያ አብዱል ቃድር ማኅበሩ በኢትዮጵያ ደረጃ የመጀመሪያው መሆኑን ገልጻለች።\n\nሳሚያ ኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ መስራችና ፕሬዝዳንት ስትሆን ተቋሙ የኢትዮጵያን ትምህርት በአዎንታዊ አስተሳሰብ ለማዘመን እንደሚሰራ ለቢቢሲ ተናግራለች።\n\nከመስራች አባላቱ መካከል አንዱ የሆነው ቀረመንዝ ካሳዬም በበኩሉ ከስድስት በላይ በስሙ የተመዘገቡ የፈጠራ ሥራዎች ያሉት መሆኑን ለቢቢሲ ገልጿል።\n\nቀረመንዝ የሥራ ፈጣሪዎች በተለያዩ ስፍራዎች በየግላቸው እየሮጡ እንደሚገኙ አስታውሶ፣ ለየብቻ መሮጣቸው ያስገኘው ይህ ነው የሚባል ውጤት አለመኖሩን በማንሳት ማኅበር ማቋቋሙ ጠቃሚ እንደሆነ ይናገራል።\n\nይህ ከስድስት መቶ በላይ የተመዘገቡ አባላት መያዙ የተገለፀው ማኅበርን መመስረት የፈለጉበትን ምከንያት ሲያስረዱም አስፈላጊው ክትትል እና እገዛ ቢደረግላቸው ጥቅማቸው ለሌሎች የሚተርፉ የሥራ ሃሳብ ፈጣሪ ወጣቶችን መደገፍ አስፈላጊ በመሆኑ ነው ይላል።\n\n\"ዓለም አሁን ለደረሰችበት ደረጃ የበቃቸው በሥራ ፈጣሪዎቿ ነው\" የሚሉት ሳሚያ እና ቀረመንዝ፣ ሕይወትን የሚያቀሉና የሚያቀላጥፉ ፈጠራዎች ባለቤት የሆኑ ወጣቶች ተገቢው ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የዓለም ተሞክሮን በመጥቀስ ይናገራሉ። \n\nበኢትዮጵያ የሥራ ፈጣሪዎች ላይ ተግዳሮቶች እንደሚበዙ የምትናገረው የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ሳሚያ፣ ከአሁን በኋላ የሚመጡ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ተመሳሳይ ችግር እንዳይገጥማቸው በማሰብ ማኅበሩ መቋቋሙን ገልጻለች። \n\nበትምህርት፣ ቴክኖሎጂ፣ በግብርና እና በሌሎች ኢትዮጵያን ዕድገት በሚያሳልጡ ዘርፎች ሁሉ የኢትዮጵያ ወጣቶች በሥራ ፈጠራ እና በሥራ ፈጠራ ሃሳብ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ የሚያመለክቱት ወጣቶቹ፤ ነገር ግን ያላቸውን ርዕይ ወደ ተግባር ላይ ለመለወጥ በርካታ ተግዳሮቶች እንደሚገጥማቸው ይናገራሉ።\n\nበመላ አገሪቱ የሚገኙ የሥራ ፈጣሪዎች በአገር ውስጥ እንዲሁም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ካሉ ባለሙያዎች ጋር ማስተሳሰር፣ ሃብቶችን ማሰባሰብ እና የክህሎት ሥልጠናን ለአባላቱ መሥጠት ከማኅበሩ አላማዎች መካከል ቀዳሚዎቹ መሆናቸውን ገልፀዋል።\n\nየሥራ ፈጣሪዎች ወደ ሥራ ፈጣራ ኮሚሽንም ሆነ ወደ ኢኖቬሽን ሚኒስቴር በተበታተነ መልኩ በመሄድ ድጋፍና እገዛ እንደሚጠይቁና ይህ ግን ለተቋማቱም ሆነ ለሥራ ፈጣሪዎቹ አስቸጋሪ መሆኑን ይናገራሉ።\n\nስለዚህ ማኅበራቸው መመስረቱ በጋራ በመሆን የሚያስፈልጓቸውን ጉዳዮች ለመጠየቅ እንዲሁም የሥራ ፈጣሪዎችን በተገቢው መልኩ ለማገዝ ይረዳል ይላሉ።\n\nየማኅበሩ ፕሬዝዳንት የሆነችው ሳሚያ አብዱል ቃድር፣ ይህ ማኅበር መቋቋሙ የሥራ ፈጣሪዎችን ውጣ ውረድ በግማሽ እንደሚቀንሰው በመግለጽ፣ ከተለያየ የመንግሥት ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት እንደሚፈልጉ ትናግራለች።\n\nእነዚህ ወጣቶች እንቅፋት በገጠማቸው ቁጥር እነርሱም ሆነ አገር ተገቢውን ጥቅምና ግልጋሎት ከማግኘት እንደሚሰናከሉ የምታስረዳው ፕሬዝዳንቷ፣ ይህ ማኅበር ሥራ ፈጣሪዎች እርስ በእርሳቸው መደጋገፍ እንዲችሉ በማሰብ የተመሰረተ ነው ብላለች። \n\nበርካታ ወጣቶች በመደበኛው ትምህርት ውስጥ የሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ሳይሆን የተቀጣሪነትን አስተሳሰብ እንዲይዙ ተደርገው መሰልጠናቸውን በማስታወስም፣ ማህበሩ ለሥራ ፈጣሪ አባላቱ የክህሎት እና ራስን የማነጽ ሥልጠናዎችን እንደሚሰጥም ተናግራለች።\n\nሳሚያ፣ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ትክክለኛ ቀጥተኛ እና ጠቃሚ የሆነ መረጃ በማግኘት ረገድ ክፍተት እንዳለባቸው ጠቅሳ፣ ማኅበራቸው በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ያለውን ክፍተት ለመድፈን እንደሚሰራም ገልጻለች።\n\nበተጨማሪም ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች፣ ስለ አዳዲስ ሕጎች፣ የሥራ ፈጠራቸውን የት ይዘው መሄድ... ", "passage_id": "a4465ea66f7367fad2f882067eb9e359" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- የማህበረሰቡን ችግር መፍታት ላይ የሚያተኩር ‹‹ሶልቭኢት›› የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድር ከ1ሺ500 በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ ለሁለተኛ ጊዜ ትናንት በይፋ ተጀምሯል፡፡በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በተደረገ ይፋ የመክፈቻ ስነስርአት ላይ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማት እና ምርምር ዳይሬክተር ጀነራል የሆኑት አቶ ካሊድ አህመድ እንደተናገሩት፤ ተወዳዳሪዎቹ ጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም መሰረታዊ የማህበረሰብ ችግሮችን የሚፈቱ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በመስራት ይሳተፋሉ፡፡ በፈጠራ ባለሙያዎቹ የሚሰሩ ችግር ፈቺ ቁሶች ወደገበያው እንዲገቡ ለማድረግ እገዛ ይደረጋል፡፡በአይኮ ግላብስ ‹‹የሶልቪት›› የፕሮጀክት አማካሪ የሆነው ወጣት ህሩይ ፀጋዬ ውድድሩን አስመልክቶ እንደገለፀው፤ በኢትዮጵያ የተሻሻለ ቴክኖሎጂን በመፍጠር የማህበረሰብን ችግር የማቃለል ልምድ ወደኋላ የቀረ ነው፡፡ ቴክኖሎጂ ቅንጦት እና ለአደጉት አገራት ብቻ  የሚሰራ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በዚህ መነሻ የቀን ተቀን ችግር ለመፍቻ እና ኢንዱስትሪዎችን ለማዘመን ይህን ውድድር ማካሄድ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በሁሉም አገሪቷ የሚገኙ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ስልጠና በመስጠት እንዲሳተፉ ይደረጋል፡፡ ሃሳባቸውንም ገበያ ላይ ሊውል ወደሚችል የቴክኖሎጂ ውጤት እንዲቀይሩ ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡በሶልቭኢት የመጀመሪያ ዙር ውድድር ላይ የኦክስጂን ቴራፒ (በደም ውስጥ ያለውን የኦክስጂን መጠን የሚለካ) ቴክኖሎጂ፣ከባህላዊ መጠጦች ከሚገኝ ተረፈ ምርት ውጤት የኤሌክትሪክ ማመንጫ ቴክኖሎጂ እንዲሁም በተለያየ ምክንያት እቃዎችን እንዳንዘነጋ የሚያስታውስ ‹‹ሄሎ ሪማይንደር›› ቴክኖሎጂን የፈጠሩ ወጣቶች አሸናፊ ሆነዋል፡፡የሁለተኛው የሶልቭኢት ውድድር በ15 ከተማዎች የሚካሄድ ሲሆን አዲስ አበባ፣ አርባ ምንጭ፣ አክሱም፣ ድሬዳዋ፣ ጎንደር፣ ጋምቤላ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ውድድሩ ከመካሄዱ በፊት ሁሉም ተሳታፊዎች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበትን መንገድ የሚያመላክት የድጋፍ ስልጠና ይወስዳሉ፡፡ ስራቸውን የሚያከናውኑበት የገንዘብ ድጋፍም ይደረግላቸዋል፡፡‹‹ሶልቭኢት›› የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድር  አሜሪካ ኤምባሲ፣ የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ እንዲሁም የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንደሚደግፉት ታውቋል፡፡አዲስ ዘመን ጥር26/2011ዳግም ከበደ", "passage_id": "050b29381ba95d929f8c84436b2df7bf" } ]
14c7587e7d2a79a010c98ea21ca5ef6a
0a2f85fd7eddba79b0bdfed188ee1622
ጁንታው ለዘረፋ ያሰማራቸውን ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር የማዋል ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የህወሓት ጁንታ ከማረሚያ ቤት በመልቀቅ ለዘረፋ ያሰማራቸውን ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር የማዋሉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ ዛሬ በመቀሌ ከተማ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።ኢዜአ እንደዘገበው፤ ምክትል ኮሚሽነር መካሉ እንደገለጹት፤ ጁንታው ከተሞችን ለቆ ከመሸሹ በፊት በማረሚያ ቤት የነበሩ ወንጀለኞችን መሳሪያ አስታጥቆ በመልቀቅ በከተሞች አካባቢ ዝርፊያ እንዲፈጽሙ አድርጓል። እነዚህ ወንጀሎችም የመንግሥት ተቋማትን ንብረት ጭምር ዘርፈዋል። የፌዴራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር የማዋሉን ሥራ አጠናክሮ መቀጠሉንም የገለጹት ምክትል ኮሚሽነሩ፤ ወንጀለኞቹ የታጠቁትን የጦር መሳሪያዎች የማስፈታቱ ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በተጨማሪም ህገ-ወጡ የህወሓት ጁንታ በመንግሥት ተቋማት ያሉ ሰነዶችንና ሰነድ የያዙ ኮምፒውተሮችን አቃጥሎ መሸሸኑም ገልጸዋል።ይህም ቡድኑ ከራሱ ስልጣን ውጭ ለህዝብ ምንም አይነት ደንታ የሌለው መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ በመጠቆምም፤ የአካባቢው ማኅበረሰብ የፌዴራል ፖሊስ እያከናወነ ያለውን ተግባር በመደገፍ ረገድ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑንም ምክትል ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37783
[ { "passage": "ዋቅሹም ፍቃዱአዲስ አበባ፡- የጁንታው ቡድን “መነሻችንና መድረሻችን አዲስ አበባ ነው” በሚል አዲስ አበባን የብጥብጥና የሁከት ቀጠና ለማድረግ አቅዷቸው የነበሩ የወንጀል ሙከራዎች በህዝቡና በፀጥታ አካላት ትብብር መክሸፋቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ::በኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት የሚዲያ ዘርፍ ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ከአገራችን ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ጁንታው በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የብጥብጥና ሁከት ሥራዎችን ለመፍጠርና ህብረተሰቡን ለማሸበር የተለያዩ ሙከራዎችን ያደረገ ቢሆንም ዕቅዶቹ የከፋ ጉዳት ከማድረሳቸው በፊት በቁጥጥር ሥር ውለዋል::የጥፋት ቡድኑ ተልዕኮውን የሚያስፈጽሙለት አካላት ከፖሊስና ከአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት ሳይቀሩ በመመልመል በየክፍለ ከተሞቹ የጥፋት ተላላኪዎችን በማሰማራት ሽብር ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት አድርጓል ያሉት ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ፤ ሆኖም የፀጥታው አካላት ከከተማው ህዝብ ጋር በመቀናጀት በሠሩት ሥራ የጁንታው የጥፋት ድግስ ሊመክን መቻሉን ጠቁመዋል::ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በርካታ ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ሥር ውለው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ በመሆኑ ለወደፊት የሚመለከተው የመንግሥት አካል ሁኔታውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ የጠቆሙት ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ፤ በአሁኑ ወቅት በቅንጅት በተሰራው ሥራ የመዲናይቱ ነዋሪዎች ያለምንም ፀጥታ ችግር ወጥተው መግባት ችለዋል ብለዋል::ዋና ኢንስፔክተሩ እንዳሉት የጁንታው ዝግጅት ከባድ ለመሆኑ በተደረገው ድንገተኛ ፍተሻና በህዝቡ ጥቆማ የተያዙ የተለያዩ ጦር መሣሪያዎች በቂ ማሳያዎች ናቸው::እስካሁን በተለያዩ ተቋማት፣ በተሽከርካሪና ቤት ለቤት በተደረጉ ፍተሻዎች ባልተለመደ መልኩ የእጅ ቦምቦች፣ የተለያዩ ጥይቶች፣ ፀረ ተሽከርካሪ ፈንጂዎች፣ አጭርና የረጅም እርቀት ወታደራዊ የሬዲዮ መገናኛ፣ የተለያዩ ሽጉጦች፣ ክላሽንኮቮች፣ ላውንቸሮችና ሌሎች በርካታ የጦር መሣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ተናግረዋል::ህዝቡ ወንጀለኞችን ለሕግ አካላት አሳልፎ ለመስጠት እንዲያግዝ በየአካባቢው የሚገኙ የፖሊስና ሌሎች የፀጥታ አካላትን የስልክ ቁጥሮች የመያዝ ባህል ማዳበር እንዳለበት ዋና ኢንስፔክተሩ ጠቁመው፤ በደል የደረሰበት ግለሰብም ሆነ ቡድን ማንኛውንም አጠራጣሪ ነገር ሲመለከት ወይም ሲያጋጥም ለፀጥታ አካላት በማሳወቅ ወንጀለኞችን አደብ የማስገዛት ሥራ ላይ ተባባሪ መሆን አለበት ብለዋል::የአዲስ አበባን ነባራዊ ሁኔታ አስመልክተው ዋና ኢንስፔክተሩ እንዳሉት መከላከያ መቀሌን ከተቆጣጠር ወዲህ የወንጀል ድርጊቶች በመጠኑ እየቀነሱ ቢሆንም ፖሊስ መደበኛውን የሕግ ማስከበር ሥራ እንደ ወትሮው እየሠራ ይገኛል:: ሆኖም የተበታተነው የጁንታው ሃይል ተለቅሞ በሕግ ቁጥጥር ሥር እስከሚውል ህብረተሰቡ ሳይዘናጋ ሰላሙን በንቃት ከመጠበቅ ጎን ለጎን ወንጀለኞችን ለፀጥታ አካላት አሳልፎ ለመስጠት ቀና ትብብሩን ማጠናከር ይጠበቅበታል::አዲስ ዘመን ታህሳስ 5/2013", "passage_id": "55f060de80f8922ba03bb87558291b0f" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 8፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከሀገር በተለያዩ መንገዶች የሸሸን ሃብት ለማስመለስ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ጠቅላይ ዓቃቢ ህግ አስታወቀ፡፡ባለፉት አመታት ከሀገሪቱ በተለያየ መንገድ በርካታ ሃብት ተመዝብሮ ወደ ውጭ ሸሽቷል።ሃብቱ ሊሸሽ የቻለውም በመንግስት መዋቅር ውስጥ በነበሩና ከእነሱ ጋር ጥብቅ ቁርኝት በነበራቸው ባለሃብቶች ትብብር እንደነበረ ይገለፃል።የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቢ ህግ አቶ ብርሁኑ ጸጋዬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2011 ዓ.ም የ11 ወራት የስራ አፈጻጸምን ሪፖርትን ሲያቀርቡ የሸሸውን ሃብት ለማስመለስ ከተወሰኑ ሀገራት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን ገልፀዋል፡፡እንዲሁም ከሌሎች ሀገራት ጋር ሃብቱን ለማስመለስ በጥንካሬ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ነበር ።ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትም ይህ የተመዘበረውን ሃብት የማስመለስ ሂደት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል ሲል ጠይቋል።ሃብቱ የተደበቀው በእነማን እና የት እንደሆነ ተልይቷል ያሉት በጠቅላይ ዓቃቢ ህግ የህዝብ ግንኙነት ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ቱሉ፥ በወንጀል የተገኘ ሃብትን የማስተዳደር ስርዓት አለመኖሩ በሂደቱ ችግር መፍጠሩን አንስተዋል፡፡ዳይሬክተሩ አሁን ላይ ሃብት የማስመለስ ዳይሬክቶሬት መቋቋሙን በመግለፅ÷ በዚህ የተሳተፉ ወንጀለኞች በህግ እንዲጠየቁ ማድረጉ በትኩረት እየተሰራበት ነው ብለዋል።ጉዳዩ ውስብስብና ጊዜ የሚጠይቅ መሆኑን ያነሱት አቶ ዝናቡ፥ የምራመራ ሂደቱ ሲጠናቀቅ በእነማን እና የት ሀገር ሃብት ሸሸ የሚለው ወደ ፊት ይፋ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ከዚህ ባለፈም በሀገሪቱ በወንጀልና በሙስና የተዘረፈን የሀገርና የህዝብ ሃብት የማስመለሱ ስራ መጠናከሩን አቶ ዝናቡ ጠቁመዋል፡፡በ2011 ዓ.ም ያለአግባብ የህዝብ ሃብትን ለራሳቸው አድርገው ያከማቹትን በማጣራትና በመለየት ከ95 ሚሊየን ብር በላይ ማስመለስ እንደተቻለ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፥ ባለፉት ሶስት ወራትም ከ35 ሚሊየን ብር በላይ ማስመለስ ተችሏል ነው ያሉት ።በጌታሰው የሽዋስ", "passage_id": "2ae20e7b1ca9a91fbc225a45d11eafab" }, { "passage": "በትግራይ ክልል የህግ ማስከበር ዘመቻ ላይ የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አባላት ባከናወኗቸው የፍተሻ ስራዎች ጁንታው አገር ማፍረስ ተልዕኮው ይገለገልባቸው የነበሩ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ተገለፀ፡፡በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ የክትትል ኦፕሬሽንና አስገዳጅ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮማንደር ጥላሁን ወልደ ትንሳኤ በትግራይ ክልል ሀገራዊ ግዳጅ ላይ የተሰማሩ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አባላት ከፍተሻ ስራ በተጓዳኝ ማህበረሰቡን የማረጋጋት ስራዎችን ማከናወናቸውን ተናግረው ሰራዊቱ ባደረገው ጥረት በክልሉ የበለጠ መረጋጋት መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡በትግራይ ክልል በመከናወን ላይ የሚገኘው ህግን የማስከበር የህልውና ዘመቻ ውጤታማ መሆኑን የገለፁት ኮማንደር ጥላሁን በተለያዩ ስፍራዎች ለእኩይ አላማ እንዲውሉ የተዘጋጁና ከሰራዊቱ እይታ የተደበቁ ረጅም ርቀት ተወንጫፊ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ዘመናዊና ኋላ ቀር መሳሪያዎች ለታለመላቸው ድርጊት እንዳይውሉ የማምከን ስራዎች ማከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡በፌደራል ፖሊስ የኮማንዶ ዲቪዥን ሻለቃ አዛዥ ምክትል ኮማንደር መሃመድ አሰፋ በበኩላቸው በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንና ማህበረሰቡ ያለ ፀጥታ ስጋት መንቀሳቀስ እንዲችል ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከሀገር መከላከያ ሰራዊትና ከሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን በመፍጠር በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ጁንታው ለፀረ-ሰላም ተግባር የሚጠቀምባቸው በግልና በቡድን የሚያዙ የጦር መሳሪያዎችና ጥይቶች በሰራዊቱ እየተያዙ መሆናቸውን የገለፁት በመቀሌ ከተማ የህግ ማስከበር ስራ ላይ የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አመራርና አባላት እነዚህን የጦር መሳሪያዎች ለመቆጣጠር በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ህብረተሰቡ የጎላ ሚና እንዳለው ተጠቁሟል፡፡", "passage_id": "7768023c027e8f9821b2e0a2d24d93f0" }, { "passage": "የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በተለያዩ ጊዜያት በሀገር ክህደት ወንጀል ተጠርጥረው መያዣ ትዕዛዝ ከአወጣባቸዉ አመራሮችና የጦር መኮንኖች መካከል በቁጥጥር ስር በዋሉት ምርመራ እያካሄደባቸው መሆኑንና በየጥሻውና በየጉድጓዱ የተደበቁትንም በማደን ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በሚያካሄዱት የህግ ማስከበር ዘመቻ በጁንታው የህወሃት ቡድን ውስጥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በመሳተፍ የጥፋት ስራው አካል ናቸው ብሎ በጠረጠራቸው ከ3 መቶ በላይ ከፍተኛ አመራሮችና የጦር መኮንኖች ላይ የመያዣ ትዕዛዝ ከፍርድ ቤት መውጣቱ ይታወቃል፡፡በዚህም እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል፡-ይህ በእንዲህ እንዳለም የመያዣ ትዕዛዝ ከወጣባቸው 81 የህወሀት ከፍተኛ አመራሮች ውስጥ ዶ/ር አዲስአለም ባሌማ የተያዘ መሆኑ ይታወቃል::የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሀገር መከላከያ እና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ባካሄዱት የተቀናጀ የህግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት በተካሄደው የምርመራ ስራ እንደተጣራው እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል፡-የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከሌሎች የፀጥታ ሀይሎች ጋር በመቀናጀት ቀሪ ያልተያዙ የጦር መኮንኖችንና የህወሀት አመራሮችን ከየተደበቁበት ጥሻ፣ ዋሻ እና የሀይማኖት ስፍራዎች በማደንና በመልቀም ለህግ ለማቅረብ ቀን ተሌት እየሰራ ይገኛል፡፡የጁንታው የህወሀት አመራሮች በውጊያ ከተሸነፉ በኃላ ራሳቸውን ካለባበስ ጀምሮ በመቀያየር ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሱ እንዳሉ ፖሊስ መረጃው ደርሶታል፡፡የትግራይ ክልል ህዝብ ህግ ለማስከበር በተደረገው ዘመቻ እስከዛሬ ላደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ኮሚሽኑ ምስጋና እያቀረበ ያልተያዙትን ተፈላጊዎች ከተደበቁበት ቦታ ይዞ ለህግ ለማቅረብ በሚያደርገው እንቅስቃሴ ከፖሊስ አባላት ጎን በመቆም እና አስፈላጊውን ጥቆማ በመስጠት የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ኮሚሽኑ ጥሪውን ያቀርባል፡፡የኢፌዲሪ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽንታህሳስ 27/ 2013 ዓ/ምአዲስ አበባ", "passage_id": "e8895826d623599484b5b6d8cebf5ceb" }, { "passage": "“ሕወሓት በትግራይ ክልል ተሰማርቶ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ሃይል ላይ ጭምር ጥቃት ከመሰንዘር ባለፈ ከፍተኛ የንብረት ዝርፊያ ፈጽሟል”-የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን\n\nከሰሞነኛ ሃገራዊ የጸጥታ ችግሮች ጋር በተያያዘ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል እንዳሻው ጣሰው እና የኮማንድ ፖስት ፕሬስ ሴክሬተሪያት አቶ ሬድዋን ሁሴን ዛሬ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።\nመንግስት በሃገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት ላይ ድንገተኛ ጥቃት ፈጽሟል ባለው ሕወሓት ላይ እየተወሰዱ ስላሉ እርምጃዎች ያብራሩት የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄነራል እንዳሻው ጣሰው “ጽንፈኛ”ያሉት የሕወሓት ኃይል ከማዕከላዊ መንግስት ጋር ለመስራት ያለመፈለግ፣ ህገ ወጥ ምርጫ ማከናወን፣ የሰራዊት ኃይል ለውጊያ በሚመጥን መንገድ ማዘጋጀት፣ የፌዴራል መንግስቱን ህገ ወጥ ነው ብሎ ባገኘው ሚዲያ በሙሉ ማሰራጨት ሌሎች ለጸጥታ ስጋት የሆኑ ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል ብለዋል፡፡\nከኦነግ/ሸኔ ታጣቂ ሃይል ጋር በመቀናጀት በተደራጀ መንገድ ከውጭ እና ከሃገር ውስጥ የሚደረግላቸውን የፋይናንስ ድጋፍ በመጠቀም ላለፉት ሁለት ዓመታት የተለያዩ የሃገሪቷን ክፍሎች ሲያተራምሱ መቆየታቸውን ለማረጋገጥ መቻሉንም ነው የገለጹት፡፡\n“በሁሉም አካባቢዎች ያጋጠሙ የጸጥታ ችግሮች በአንድም በሌላ መንገድ ሲያደራጁ ሲመሩ የነበሩ መሆናቸውን ምርመራዎቻችንና መረጃዎቻችን በአግባቡ አረጋግጠዋል” ብለዋል ኮሚሽነር ጄነራሉ፡፡\nየፌዴራል ፖሊስ ባለው ህገመንግስታዊ ተልዕኮ በሁሉም የሃሪቱ ክፍል ተሰማርቶ የህዝቡን ሰላምና ጸጥታ የሚጠብቅ ኃይል ነው፡፡\nበትግራይም በ22 ትልልቅ ተቋማት ውስጥ ስምሪት አድርጎ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ ተቋም ነው እንደ ኮሚሽነር ጄነራሉ ገለጻ፡፡\nሆኖም “ህዝቡን ሲያግዝ በነበረበት ወቅት ህወሓት ከፍተኛ ሃይል በመመደብ ጥቃት ሰንዝሮበታል ከነዚህ ተቋማትም ከፍተኛ የንብረት ዝርፊያ ፈጽሟል”፡፡\nሰራዊቱም ራሱን ለመከላከል አንዳንድ ስራዎችን ከመስራት በተጨማሪ ከትግራይ ህዝብ ጋር ሆኖ ራሱን ተከላክሏል፡፡\nእንደ ኮማንድ ፖስቱ ፕሬስ ሴክሬተሪያት አቶ ሬድዋን ሁሴን ገለጻ ሰራዊቱ የውጊያ ዓላማ ሳይኖረው ህብረተሰቡ የሚገለገልባቸውን የሲቪል ተቋማት ሲጠብቅ የነበረ ነው፡፡ ሆኖም ከጥቃት አላመለጠም፡፡\nፕሬስ ሴክሬተሪያቱ “የተጀመረው የጋራ ተቋማቶቻችንን በመጉዳትና በማፍረስ አብሮነታችንን አደጋ ላይ የሚጥል ትንኮሳ ነው” ያሉም ሲሆን መንግስት ህግ የማስከበር እና ህገ መንግስቱን የማጽናት ስራ እንዲሰራ የተገደደበት ሁኔታ ነው መፈጠሩን አስታውቀዋል፡፡\nፅንፈኛው የሕወሓት ቡድን በትላልቅ የሃገሪቱ ከተሞች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ኃይል እንዳሰማራ መረጋገጡንም መግለጫውን ዋቢ አድርጎ የተሰራው የኢቢሲ ዘገባ ያሳያል፡፡\nትናንት በትግራይ ቴሌቪዥን በቀጥታ በተላለፈ መግለጫ ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያብራሩት የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) “በትግራይ ህዝብ ላይ ጦርነት ያወጁ የሩቅና የቅርብ ጠላቶችን ለመደምሰስ በሚያስችል ሙሉ ቁመና ላይ እንገኛለን”ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ነው፡፡\n", "passage_id": "806d5d49717c4159087f184483cf0775" } ]
ee513b92306a9ccfeeec02f0313c16cd
72ce3520235e92db5c4defc40866fd86
ኦነግ ሸኔን በመደምሰሱ ሂደት የህዝቡ ድጋፍ ትልቅ ድርሻ እንደነበረው ተገለጸ
ዋቅሹም ፍቃዱ አዲስ አበባ፡- በሰላም ለመታገል ወደ አገር ውስጥ ከገባ በኋላ ወደ ትጥቅ ትግል የተመለሰው ኦነግ ሸኔን በመደምሰስ ሂደት ህዝቡ ከጸጥታ አካሉ ጎን ሆኖ በአሰሳ እያገዘ፤ በሰላማዊ ሰልፍም ቡድኑን እያወገዘ መሆኑ ተገለጸ።ከመስከረም 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በተወሰደው እርምጃ 846 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ፤ ከ3ሺህ 700 በላይ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ሆነው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑንም የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ተናግረዋል። ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የኦነግ ሸኔ ቡድን ኃይሉን ለማጠናከር በክልሉ ጠረፋማ አካባቢዎች ተደብቆ የጥፋት ኃይሎችን በመመልመል ሲያሰለጥን፤ እንዲሁም በህወሓት ጁንታ ኃይል የሎጀስቲክ ድጋፍ ተደርጎላቸው በትግራይ ክልል ጭምር በመሄድ ስልጠና ሲወስድ ነበር። አሁን ላይ ግን ጁንታው በመደምሰሱ የቡድኑ ኃይል እየተዳከመ ከመሆኑ በተጨማሪ፤ ባለፉት ሦስት ወራት የክልሉ መንግሥት ህዝቡን በጎኑ በማሰለፍ በወሰደው እርምጃ 413 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እጅ ባለመስጠታቸው ሲገደሉ፤ እጅ የሰጡና የተያዙ ደግሞ 433 ናቸው። በዚህም በጥቅሉ 846 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተደምስሰዋል።የኦነግ ሸኔ ቡድን እጅግ ጨካኝ ከመሆኑ የተነሳ ስልቱን በመቀያየር አንዳንድ አካባቢዎች እንደ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ በብሔር ላይ ያነጣጠሩ ጥቃት ይፈጽማል፤ በምስራቅ ኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ሀይማኖታዊ መልክ ያለው ጥቃት በመፈጸም አገርን ለማተራመስ ይጥራል። በዚህ መልኩ እስካሁን መንግሥት ሹመኞችና በንጹኃን ዜጎች ላይ በወሰዳቸው እርምጃዎችም ከ500 በላይ ንጹኃን ህይወታቸውን አጥተዋል።አሁን ግን አንዳንድ እንደ ቄለም ወለጋ ያሉ አካባቢዎች ህዝቡ ወጥቶ አሰሳ እያደረገ፣ በሠላማዊ ሰልፍም እያወገዘ በመሆኑ እንደ ከዚህ በፊቱ ጉልበቱን አጠናክሮ የጥፋት ስራውን መፈጸም አይችልም። እንደከዚህ በፊቱም መንገድ ዝጉ እንዲ አድርጉ የሚሉ ትዕዛዞችን ህዝቡ እየተቀበለ አይደለም። የክልሉ ጸጥታ አካላትም ቡድኑ የሚንቀሳቀስበት አካባቢን ተቆጣጥረው እንዳሉ፤ እና ህዝቡም የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ነው ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ የተናገሩት።እንደ ኦነግ ሸኔ ቀጥታ ጠመንጃ አንግበው ህዝቡን የሚጨርሱና ተኩሰው ባይገሉም ኦነግ ሸኔን በቁሳቁስ፣ በገንዘብና በሞራል የሚደግፉ እንዲሁም ኦነግ ሸኔ የሚፈጽመውን ጥቃትና ጥፋት ወደ መንግሥት በማዞር በተሳሳተ መረጃ ህዝቡን የሚያደናግሩና መንግሥትን በተለይ የጸጥታ ኃይሉን ለማጠልሸት በኦነግ ሸኔ የተደራጁ በርካታ የሶሻል ሚዲያ ሠራዊት ጭምር መኖራቸውን የጠቆሙት ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ፤ በዚህ መሰል ጥፋት የተሰለፉ ከ3ሺህ 700 በላይ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ሆነው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም ከመንግሥት መስሪያ ቤት ሳይቀር ሰፊ የማጥራት ስራ ለመስራት በቅርቡ እንደሚጀመር ተናግረዋል። ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዘው አገሪቱን የብጥብጥ ቀጠና ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት 1ሺህ 700 በላይ በተለያዩ የስልጣን እርከን ላይ በነበሩት አመራሮች ላይ የተወሰደው እርምጃ አሁን በኦነግ ሸኔ ላይ እየተወሰደ ላለው እርምጃ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የገለጹት ኮሚሽነር አራርሳ፤ በወቅቱ የተተኩ አዳዲስ አመራሮች በቁርጠኝነት የሰሩት ሥራ ኦነግ ሸኔን ለማድከም ትልቅ አስተዋፅዖ እንደነበረው ገልጸዋል። ህዝቡም ቡድኑን አሳልፎ በመስጠትና ለጸጥታ አካላት መረጃ በማቀበል ጉልህ ሚና መጫወቱንም አብራርተዋል።እንደ ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ገለጻ፤ በዓለም ተሞክሮ ሽምቅ ተዋጊ ኃይል በአንድ ቦታ ሆኖ በግንባር የሚዋጋ ኃይል ባለመሆኑ በአንድ ጀምበር ማጥፋት ሊያዳግት ይችላል። ሆኖም ሁለት መሠረታዊ ስልቶችን በመጠቀም በድኑን ከነ ዓላማው መቅበር ይቻላል። አንደኛው፣ በህዝቡ ላይ በመስራት የጥፋት ቡድኑን ብቻውን በማስቀረት ተስፋ ቆርጦ እንዲጠፋ ማድረግ ወሳኝ ስልትና ትልቁ የመንግሥት የቤት ስራ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ሁሉንም የድጋፍ በሮችን በመዝጋት የሎጅስቲክ ረሃብተኛ፣ ከዓለም የተነጠለ፣ ከህዝብ የተገለለ በማድረግ ይህን የሽምቅ ተዋጊ ቡድንን ከስራ ውጭ ማድረግ ይቻላል። በዚህ መልኩም እየተሰራ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12 ቀን 2013  ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37765
[ { "passage": " • ምክትል ሊቀ መንበሩን ጨምሮ 6 አመራሮች ታግደዋል • የታገዱት አመራሮች ኦነግን እያደስን እንሄዳለን ብለዋል በኦነግ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሣና  ም/ሊቀመንበሩን ጨምሮ በሌሎች ከፍተኛ አመራሮች መካከል ውዝግብ መፈጠሩ ታውቋል፡፡ ውዝግቡ የተፈጠረው ከሰሞኑ የድርጅቱ ሊቀ መንበር 6 የፓርቲው አመራሮችን ማገዳቸውን ተከትሎ ነው፡፡   የኦነግ ቃል አቀባይ አቶ ቀጄላ መርዳሳ ለአዲስ አድማስ በሰጡት ማብራሪያ፤ ድርጅቱን የማዳከም እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ በሊቀመንበሩና በሌሎች የፓርቲው አመራሮች መካከል አለመግባባት መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡  ሊቀ መንበሩ የድርጅቱን አመራሮች በፌስቡክ በተሰጠ መግለጫ አግጃለሁ ማለታቸው ከፓርቲው ህገ ደንብ ውጪ የሆነ አካሄድ በመሆኑ ሁላችንም በመደበኛ ስራችን ላይ እንገኛለን ብለዋል፤ አቶ ቀጄላ፡፡ \"እንኳን አመራርን ቀርቶ ተራ አባልንም ከፓርቲ ለማባረር ህገ ደንብን መሠረት ተደርጐ ነው\" ያሉት ቃል አቀባዩ፤ \"ነገሩ ቀልድ ነው፤ ድርጅቱን ለማዳከምና ለመከፋፈል የተደረገ ጥረት አካል ነው\" በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡  #እኔ ካልመራሁ ምንም ስራ መሠራት የለበትም በሚል ድርጅቱን ለማዳከም ጥረት እየተደረገ ነው፤ ይሄ ደግሞ ህገ ወጥና ስርአት አልበኝነት ነው; ሲሉ የነቀፉት አቶ ቀጄላ፤ #አግደናል የተባለውንም እኛ አንቀበለውም; ሲሉ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡ የኦነግ ም/ሊቀመንበር አቶ ቢቂላ አራርሶ፣ ቃል አቀባዮቹ አቶ ቀጀላ መርዳሣና አቶ ቶሌራ ኡዳባን ጨምሮ 6 ሰዎች መታገዳቸውን የገለፁት የኦነግ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሣ በበኩላቸው፤ ጉዳዩ በፓርቲው የህግ ክፍል የተያዘ በመሆኑ ማብራሪያ ለመስጠት አልችልም ብለዋል፡፡   በሌላ በኩል፤የኦነግ ም/ሊቀመንበር ቢቂላ አራርሶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኦነግ ከህወሓትም ሆነ ከኦነግ ሸኔ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለው ጠቁመው፤ በዚህ ሰበብ በአባላቶቻችን ላይ የሚፈፀመው እስራትና ወከባ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባዋል ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ በአመራር ውዝግብ ውስጥ መግባቱ በተደጋጋሚ እየተገለፀ ያለው ኦነግ፤ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ #ከህወሓትና ኦነግ ሸኔ ጋር ትሠራላችሁ; የተባሉ ከ600 በላይ አባሎቹና አመራሮቹ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለእስር መዳረጋቸውን አስታውቋል፡፡ ግንባሩ አገራዊ ወቅታዊ ሁኔታውን ገምግሞ ሰሞኑን ባወጣው መግለጫው፤ #በህዝብና በመንግስት መካከል ልዩነትን በማስፋት ወደ ስልጣን ለመምጣት የሚደረግን ጥረት እቃወማለሁ፤ በዚያው ልክ መንግስት ዲሞክራሲያዊ ስርአትን እገነባለሁ ሲል የገባውን ቃል ተግባራዊ ሊያደርግ ይገባል; ብሏል፡፡ የኦነግ ም/ሊቀመንበር ቢቂላ አራርሶ፣ የኦነግ ቃል አቀባዮቹ አቶ ቀጄላ መርዳሣና አቶ ቶሌራ ኡዳባ በጋራ በሰጡት በዚህ መግለጫ፤ ኦነግ የሀገሪቱን ህግ በማክበር ድርጅቱን በማደስ ይበልጥ ዲሞክራሲያዊ፣ አሣታፊና ሁሉን ህብረተሰብ ያቀፈ እንዲሆን እየተሠራ መሆኑንም አብራርቷል፡፡  በኢትዮጵያ ጉዳይ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በአንድነት ለመስራት በአዲስ እቅድ መነሳቱንም ያስታወቀው ኦነግ፤ አሁን በሀገሪቱ ጉዳይ ላይ ሁነኛ ምክክር ማድረግ ያስፈልጋል ብሏል፡፡ ድርጅቱ ከታጣቂ ሃይሎችና ከህወሓት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለው የጠቆመው መግለጫው፤ የኦነግ ሸኔ መዋቅርም በኦነግ እውቅና የሌለው ነው ብሏል፡፡ “ከህወኃት ጋር የመጠራጠርና የስጋት እንጂ የትብብርም ሆነ አብሮ የመስራት ታሪክ የለኝም” ያለው ኦነግ፤ በዚህ ሰበብ ከ600 በላይ አመራርና አባላቱ መታሠራቸው አግባብ እንዳልሆነ በማመልከትም፤ ከእስር እንዲለቀቁና በሀገሪቱ የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ውስጥ በጐ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቋል፡፡  ለአገሪቱ ወሳኝ የሆነውን ሠላም ለማረጋገጥ የህዝቡን አንድነት የሚያጠናክር ስራ ሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች እንዲሰሩም  ጥሪ አቅርቧል፤ ኦነግ በመግለጫው፡፡ ", "passage_id": "4fc65b68b4986b5750b8158c1adf077f" }, { "passage": "አዲስ አበባ :- ኦነግ ኦዴፓና የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነትና አንድነት ለማረጋገጥ በጋራ እንደሚሰሩ አስታወቁ።በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው በሃገር ውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የኦነግ ታጣቂ ወደ ካምፕ ለማስገባት በመንግሥት፣ በኦነግ የዕርቀ ሰላም ኮሚቴና በሃገር ሽማግሌዎች አማካኝነት፥ ስለተሰራው ሥራ የማጠቃለያ ሪፖርት ላይ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የኦነግ አመራሮች፥ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነትና አንድነት ለማረጋገጥ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን ተናግረዋል።ኦነግ የክልሉ መንግሥት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚሰራቸውን ስራዎች እንደሚደግፍና ከዚህ በኋላ ታጥቆ የሚንቀሳቀስ ሰራዊት እንደማይኖር ሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ተናግረዋል።(ምንጭ፡- ኤፍ.ቢ ሲ)አዲስ ዘመን ግንቦት 23/2011", "passage_id": "8ecd42f29ac80b352cdd6a8684561237" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅ ወለጋ ዞን አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው ሰላም እንዲረጋገጥ ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረው እንደቀሚቀጥሉ ተገለፀ ።በነቀምት ከተማ የዞን እና የወረዳ መስተዳድርና የፀጥታ አካላትን ጨምሮ ከምዕራብ ዕዝና ከፌደራል ፖሊስ የተውጣጡ አመራሮች በጋራ መክረዋል።ወይይቱን የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አስመራ ኢጃራ፣ የምዕራብ ዕዝ ኢንዶክትሪኔሽን እና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር እና የዞኑ የፀጥታ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኮለኔል ተስፋዬ ነጋሽ እንዲሁም የምዕራብ ኦሮሚያ ልዩ ሀይል አዛዥ ረዳት ኮሚሽነር ጋሊ ከማል መርተውታል፡፡አቶ አስመራ ኢጃራ እንደገለፁት ኦነግ ሸኔ በዞኑ ብዙ ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ተከትሎ  መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።ኮለኔል ተስፋዬ ነጋሽ በበኩላቸው ሰራዊቱ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የፀረ ሰላም እንቅስቃሴ የሚታይባቸውን አካባቢዎች በመለየትና የተጠኑ የፀረ ሽምቅ ስምሪቶችን በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን እየሰራ መምጣቱን ጠቁመዋል ።ረዳት ኮሚሽነር ጋሊ ከማል ጥፋት የሚያደርሱ ቡድኖችን እስከነ ሴላቸው ተከታትሎ ከመደምሰስ ባሻገር  የሚያገኛቸውን ድጋፎች በማቋረጥ የተሰራው ስራ ጥሩ እንደሆነ መናገራቸውን የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ያወጣው መረጃ ያመለክታል።", "passage_id": "8362734dc9e4b5bd693e529915d47f69" }, { "passage": "የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እርስ በእርስ ባለመግባባት በእነ አቶ አራርሶ ቢቂላ እና በእነ አቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመሩ የሚባሉ ቡድኖች መፈጠራቸው ይታወሳል፡፡\nበሁለቱ ግለሰቦች የተጻፉ ደብዳቤዎችም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገቢ መሆናቸውን ቦርዱ መግለጹ ይታወሳል፡፡\nበጉዳዩ ላይ አል ዐይን አማርኛ ከኦነግ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ቀጀላ መርዳሳ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡ ኃላፊው ሦስተኛ አካል ወደ አንድ ካላመጣ በስተቀር ከእነ አቶ ዳውድ ኢቢሳ ጋር መነጋገር እንደማይችሉ ገልጸዋል፡፡ ሁለታችሁም ኦነግ እኛ ነን እያላችሁ ነው ማነው ኦነግ በሚል ለቀረበላች ጥያቄ “ ማዕከላዊ ኮሚቴው የተበታተነ ነው፣ ከሥራ አስፈጻሚ ግን ከአቶ ዳውድ በስተቀር ሁሉም ከእኛ ጋር ናቸው“ብለዋል፡፡\nከእነ አቶ ዳውድ ኢብሳ ቡድን ጋር ያሉት አቶ በቴ ኡርጌሳ ከአል ዐይን ጋር በነበራቸው ቆይታ የእነ አቶ አራርሶ ቢቂላ ቡድን የብልጽግናን አላማ እያራመዱ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አል ዐይን የጠየቃቸው የእነ አቶ አራርሶ ቡድን አባል አቶ ቀጀላ መርዳሳ ይህ ተራ የሥም ማጥፋት ዘመቻ እንደሆነ ገልጸው“ ይህ የእነ አቶ ዳውድ የቆየ የፖለቲካ ሴራ ነው፤ከዚህ ቀደምም የሰው ስም ሲያጠለሹ ነበር፣ ስለዚህ ይህ ላለፉት 20 ዓመታት በላይ የተካኑበት በመሆኑ ጆሮ አንሰጠውም “ ሲሉ መልሰዋል፡፡\nአቶ ዳውድ ኢብሳ ከእርሳቸው በሃሳብ ያፈነገጡ ሰዎች ከፖለቲካ እንዲርቁ የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ነው አቶ ቀጀላ የገለጹት፡፡ እናም ዛሬ እኛ ከእነ አቶ ዳውድ ጋር ስለተጣላን የስም ማጥፋት ዘመቻ እያካሄዱብን ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡\nአቶ በቴ ኡርጌሳ እነ አቶ አራርሶ ቢቂላ ከድርጅት ሥነምግባር ስላፈነገጡ እንዲወጡ ተደርጓል ያሉ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንኙነቱ ከእነ አቶ አራርሶ ቢቂላ ጋር ሳይሆን ከእኛ ጋር ነው ብለዋል፡፡ አቶ ቀጀላ ደግሞ እነ አቶ ዳውድ ኢብሳ ከድርጅቱ ታግደዋል ያሉ ሲሆን አሁን ላይ ድርጅቱ በአቶ አራርሶ እየተመራ ነው ብለዋል፡፡\nአቶ በቴ ግን አሁንም አቶ ዳውድ ኢብሳ የኦነግ ሊቀ መንበር ናቸው ሲሉ ለአል ዐይን ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይ ምን እየተካሄደ እንደሆነ እንደማያውቁ የገለጹት አቶ በቴ አቶ ዳውድ አሁን በቤት ውስጥ ሲሆኑ ወደእርሳቸው ጋር መግባትም ሆነ መውጣ እንደማይቻል አስታውቀዋል፡፡\nየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይህንን አለመግባባት ለመፍታት በእነ አቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመረጥ አንድ በእነ አቶ አራርሶ የሚመረጥ አንድ እንዲሁም በባለጉዳዮቹ የሚመረጡትን ባለሙያዎች በሰብሳቢነት የሚመራ ሌላ አንድ ባለሙያ ቦርዱ መርጦ በመመደብ የባለሙያዎች ጊዜያዊ ጉባዔ እንዲቋቋም መወሰኑ ይታወሳል፡፡\nበዚህም መሰረት በሁለቱ አካላት እና በቦርዱ የተመረጡ ባለሞያዎች ጉዳዮን አጣርተው በሚያቀርቡት የውሳኔ ሃሳብ ላይ ተመስርቶ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑንም ቦርድ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ገልጿል፡፡\n\n\n", "passage_id": "867a79c32f7956be57faa8b5c764c300" }, { "passage": "የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን እዚያው ወለጋ የተማሩት ዳውድ ኢብሳ የሁለተኛ ደረጃ ትምህረታቸውን ለመከታተል ወደ አዲስ አበባ አምረተዋል። \n\nአዲስ አበባ ከደረሱ በኋላ ጀነራል ዊንጌት ትምህርት ቤትን ተቀላቀሉ። ከጀነራል ዊንጌት በኋላ የቀድሞውን ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በመግባት የስታትስቲክስ ትምህርት መከታተል ጀመሩ። \n\n• ከ2000 በላይ ሰልጣኝ ፖሊሶች የጤና እክል ገጥሟቸው ወደ ሆስፒታል ተወሰዱ \n\n• በአዲስ አበባ ከጸጥታ ኃይሎች ጋር ባጋጠመ ግጭት 5 ሰዎች ተገደሉ \n\n• የቡራዩ ተፈናቃዮች በምስል\n\nበዩኒቨርሲቲው ቆይታቸው በንጉሡ የአስተዳደር ዘመን በነበረው የተማሪዎች ንቅናቄ ውስጥ ተሳታፊ ነበሩ። \n\nበ1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ ሱዳን በመሰደድ የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባርን የተቀላቀሉት ዳውድ፤ በስደት ላይ ሳሉ የአንድ ዓመት ወታደራዊ ስልጠና ከወሰዱ በኋላ ወደ ሃገር ቤት በመመለስ በወለጋ አካባቢ ይንቀሳቀስ የነበረውን የኦነግ ጦር መምራት ጀመሩ። \n\nብዙም ሳይቆዩ በደርግ ባለስልጣናት ዕይታ ውስጥ ገቡ። ዳውድ ኢብሳ እሳቸውን ጨምሮ 9 የቅርብ ጓደኞቻቸው በደርግ አማካኝነት መመረዛቸወን ለቢቢሲ ተናግረዋል። \n\nየተቀሩት ጓደኞቻቸው ህይወታቸው ሲያልፍ የእሳቸው ነፍስ ብቻ መትፏን ይናገራሉ። የዳውድ ኢብሳ አብሮ አደግ ጓደኛ የሆኑት ዶ/ር ደገፋ አብዲሳ፤ ዳውድ ኢብሳ በባህሪያቸው ብዙ ምግብ ስለማይመገቡ ነው ህይወታቸው የተረፈው ሲሉ ተናግረዋል። \n\nኋላ ላይ ዳውድ 1970ዎቹ አጋማሽ በደርግ ቁጥጥር ሥር ዋሉ። ለአራት ዓመታትም በእስር ቆይተዋል። በእስር ላይ ሳሉ ከፍተኛ የጤና መታወክ ይገጥማቸው እነደነበርም ያሰታውሳሉ። \n\nለህክምና ወደ ጤና ተቋም በሚመላለሱበት ወቅት በሃኪሞች አማካኝነት ከእስር ማምለጥ ችለዋል።\n\nከደርግ እስር ካመለጡ በኋላ ወደ ኤርትራ በማቅናት በድጋሚ ኦነግን ተቀላቀሉ። በወቅቱም የኦነግ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሆነው ተመረጡ። \n\nበሽግግር መንግሥቱ ወቅት ከኢህዴግ ጋር ሳይስማሙ በመቀረታቸው ወደ ኤርትራ ተመልሰው ለረዥም ዓመታት በዚያው ቆይተዋል። \n\nስለ አቶ ዳውድ ኢብሳ እውነታዎች\n\nበስድሳዎቹ መጀመሪያ በቀዳማዊ ሃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ንቅናቄ ተሳታፊ ነበሩ።\n\nየኦሮሞ ነፃነት ግንባር ከተመሰረተ ጀምሮ የግንባሩ ደጋፊ ነበሩ።\n\nየእድገት በህብረት ዘመቻ ተሳታፊም ነበሩ።\n\nከዘመቻ መልስ የኦነግ ማእከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው ተመረጡ።\n\nከእስር እንደተለቀቁ በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸው ቢመለሱም ወዲያው አቋርጠው ወደ ሱዳን በመሄድ ወታደራዊ ስልጠና ወስደው የኦነግን ትግል ተቀላቀሉ።\n\nበኢትዮጵያ የሽግግር መንግስት ተቋቁሞ በነበረበት ወቅት የግንባሩ ወታደራዊ ክፍል አዛዥ የነበሩ ሲሆን በኋላም እንደገና ወደ ኤርትራ በመሄድ መቀመጫቸውን በዚያ በማድረግ ትግል ቀጥለዋል።\n\n ", "passage_id": "b89f0ca607db95a6427ef68737758b01" } ]
12e8966685d5d855f752e32098dc605a
d1f2d1c8625e3d101bc6d32219aa38bb
ባንኩ እአአ 2020 መጨረሻ ከግብር በፊት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማትረፉን ገለጸ
ሞገስ ጸጋዬአዲስ አበባ፡- እየተጠናቀቀ ባለው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ ከግብር በፊት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማትረፉን፤ ይሄም ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በበጀት ዓመቱ የትርፍ መጠኑ የ6ነጥብ9 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ አስታወቀ። ባንኩ ለተለያዩ ሀገራዊ ልማቶች 19 ሚሊየን ብር ድጋፍ ያደረገ ማድረጉንም ተገልጿል።የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር ዶክተር ሰውአለ አባተ፣ ትናንት በአዲስ አበባ ባካሄደው የባንኩ ባለአክሲዮኖች 11ኛ መደበኛ እና 4ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የበጀት ዓመቱን ሪፖርት ለባለ አክሲዮኖች አቅርበዋል። በወቅቱም እንደተናገሩት፤ የበጀት ዓመቱ ለባንኩ ዘርፍ በርካታ እንቅፋቶች የነበሩበት ቢሆንም፤ እነዚህን ችግሮች በመቋቋም እአአ በ2020 ከታክስ በፊት የ582 ነጥብ 04 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘት ተችሏል።እንደ ዶክተር ሰውአለ ገለጻ፤ ባንኩ የውጭ ንግዱ 111 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ያስገኘ ሲሆን፤ ከውጭ ሀገር በሀዋላ እና በስዊፍት የተላከ ደግሞ የ28ነጥብ4 ሚሊዮን ዶላር አስገኝቷል። የባንኩ ሀብትም በበጀት ዓመቱ የ4ነጥብ37 ቢሊዮን ብር እድገት በማሳየት ጠቅላላ ሃብቱን ወደ 18ነጥብ87 ቢሊዮን ብር አሳድጓል።ዶክተር ሰውአለ እንደሚሉት፤ በተጠቀሰው በጀት ዓመት የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን በ3ነጥብ29 ቢሊዮን ብር በማሳደግ የባንኩን አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን 13ነጥብ88 ቢሊዮን ደርሷል። ከአጠቃላይ የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ ውስጥ የተንቀሳቃሽ ሂሳብ የ19 በመቶ ድርሻን ሲይዝ፤ በአንፃሩ የጊዜ ገደብ ተቀማጭ ደግሞ የ5 በመቶ ድርሻ ነበረው። ይህም የባንኩን አብዛኛው ተቀማጭ አስተማማኝ እንዲሆን አድርጎታል። ባንኩ በዓመቱ ውስጥ ለተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች 3ነጥብ29 ቢሊዮን ብር ብድር የሠጠ ሲሆን፤ ይህም ባንኩ አጠቃላይ የሰጠውን ብድር በ40 በመቶ አሳድጎታል።ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ባንኩ ትርፍ የብር 42ነጥብ99 ሚሊዮን ወይንም የ6ነጥብ9 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን የገለጹት ሊቀመንበሩ፤ ለዚህ ደግሞ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴውን ማቀዛቀዙ ግንባር ቀደምትነት ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በአገሪቱ በአንዳንድ ክልሎች ተከስቶ የነበረው ማህበራዊና ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ኢኮኖሚውን በጤናማ መንገድ እንዳይጓዝ በማድረግ በወጭና በገቢ ንግዱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩ ባንኩ በበጀት ዓመቱ ለማሳካት ያሰበውን የትርፍ መጠን ባሰበው ልክ እንዳይሆን ማድረጉንም ጠቁመዋል።ባንኩ በ2030 በሀገራችን ሦስት ግንባር ቀደምና ተመራጭ ባንኮች መካከል አንዱ መሆንን አላማ አድርጎ ተነስቷል ያሉት ሊቀመንበሩ፤ የቡና ባንክ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት እንደ ‹‹ገበታ ለሀገር›› የመሳሰሉ ሀገራዊ የልማት እና ኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከላከል የሚሆን ድጋፍ በማድረግ በድምሩ 19 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል። ይህ ማህበራዊ ኃላፊነትን መወጣት ቀጣይነት እንደሚኖረው በመጥቀስም፤ 37 አዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት ቁጥሩን ወደ 242 አሳድጎ በመስራት በበጀት ዓመቱ ብቻ የተቀማጭ ሂሳብ የደንበኞችን ቁጥር በ268 ሺህ70 በማሳደግ የደንበኞችን ቁጥር 809 ሺህ 493 ማድረስ መቻሉ ዓመልክተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37782
[ { "passage": "የግል ባንኮች የተቀማጭ ገንዘብ በአንድ ዓመት ውስጥ በ27.6 በመቶ በመጨመር 124.1 ቢሊዮን ብር ደረሰ፡፡የባንኮቹ የ2008 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ግርድፍ መረጃ እንሚጠቁመው፣ በ2007 ዓ.ም. የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 97.24 ቢሊዮን ብር የነበረው የተቀማጭ ገንዘባቸው መጠን፣ በዘንድሮ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የ26.9 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳይቷል፡፡በ2008 ዓ.ም. ሩብ ዓመት መጨረሻ ላይ ባንኮቹ ከደረሱበት ከጠቅላላው ተቀማጭ ገንዘብ ውስጥ 77.3 ቢሊዮን ብር የሚሆነው በቁጠባ የተቀመጠ ሲሆን፣ በጊዜ ገደብ የተቀመጠው ደግሞ 12.9 ቢሊዮን ብር ነው፡፡ በተቀማጭ ገንዘብ መጠናቸው ብልጫ ያላቸው ሦስት ባንኮች ደግሞ አዋሽ፣ ዳሸንና ሕብረት ባንኮች ናቸው፡፡አዋሽ ባንክ አምና በተመሳሳይ ወቅት የነበረውን 15.9 ቢሊዮን ብር የተቀማጭ ገንዘቡን መጠን፣ በ2008 ዓ.ም. ሩብ ዓመት መጨረሻ ላይ 19.5 ቢሊዮን ብር ሲያደርስ፣ ዳሸን ባንክ ደግሞ አምና በመጀመሪያው ሩብ ዓመት መጨረሻ ላይ የነበረውን 17.8 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ በ2008 ዓ.ም. ሩብ ዓመት ወደ 20.19 ቢሊዮን ብር ማድረስ ችሏል፡፡ ከሁለቱ ባንኮች ቀጥሎ ተቀማጭ ገንዘቡን በከፍተኛ መጠን ያሳደገው ሕብረት ባንክ ነው፡፡ ሕብረት ባንክ በ2007 በጀት ዓመት መጨረሻ ላይ 9.7 ቢሊዮን ብር የነበረውን ተቀማጭ ገንዘብ በ2008 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ 12.3 ቢሊዮን ብር አድርሷል፡፡ እንደ መረጃው እስከ 2008 ዓ.ም. ሩብ ዓመት መጨረሻ ድረስ ሁሉም የግል ባንኮች የሰጡት ብድር መጠን ደግሞ 80.2 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ ባንኮች ከሚሰጡት ከእያንዳንዱ ብድር ላይ 27 በመቶ በማስላት ለቦንድ ግዥው እንዲያውሉ በሚያስገድደው መመርያ መሠረት፣ እስካሁን ለቦንድ ግዥው ያዋሉት የገንዘብ መጠን 37.86 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡ በመረጃው መሠረት መመርያው ተግባራዊ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ እ.ኤ.አ. እስከ ሴፕቴምበር 2015 ድረስ ለቦንድ ግዥው ከዋለው ከ37.86 ቢሊዮን ብር ውስጥ፣ ዳሸን ባንክ የ6.26 ቢሊዮን ብር የቦንድ ግዥ በመፈጸም ቀዳሚ ሆኗል፡፡ ንብ፣ ሕብረት፣ ወጋገንና አዋሽ ባንኮች ደግሞ ከአራት እስከ 4.5 ቢሊዮን ብር የሚደርስ የቦንድ ግዥ ፈጽመዋል፡፡አነስተኛ የቦንድ ግዥ ከፈጸሙት ውስጥ ደቡብ ግሎባል ባንክ ተጠቃሽ ሲሆን፣ ባንኩ እስካሁን ለቦንድ ግዥው ያዋለው 26.14 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ሌሎቹ ከ370 ሚሊዮን ብር እስከ 3.7 ቢሊዮን ብር የቦንድ ግዥ የፈጸሙ ናቸው፡፡ አምስት የግል ባንኮች ከአምስት ቢለዮን ብር በላይ የቦንድ ግዥ ፈጽመዋል፡፡ ስድስቱ ደግሞ ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ለቦንድ ግዥ ማዋላቸውን መረጃው ያሳያል፡፡ግርድፍ ሪፖርቱ ሁሉም ባንኮች በአትራፊነት መቀጠላቸውን ያመለክታል፡፡ 17 የግል ባንኮች በጥቅል የነበራቸው ከ11.3 ቢሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ካፒታል ዕድገት አሳይቶ 13.2 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡", "passage_id": "809996dd97dc8466011c452b33bf36f4" }, { "passage": "ከግል ባንኮች ቀዳሚውን የገበያ ድርሻ ይዞ የዘለቀው አዋሽ ባንክ፣ በ2012 የሒሳብ ዓመት ከታክስና ከሌሎች ተቀናሾች በፊት ከ4.19 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ፡፡ ይህ ትርፍም ከግል ባንኮች የመሪነት ሥፍራ በመያዝ እንዲቀጥል አድርጎታል፡፡ የ2012 የሒሳብ ዓመት የባንኩን አፈጻጸም የተመለከቱ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ ተመዝግቧል፡፡  ባንኩ በሒሳብ ዓመቱ ይህንን ያህል ትርፍ ያስመዘገበው በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት፣ በብድር ወለድ ምጣኔዎች ቅናሽ አድርጎ ጭምር መሆኑ ተገልጿል፡፡ በኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያ የተወሰዱ ዕርምጃዎች ከወለድ የሚገኘውን ገቢ በተወሰነ ደረጃ ቢቀንሱም፣ አሁንም የግል ባንኮች ቀዳሚ የተባለውን ትርፍ ይዞ መቀጠሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡  በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት አዋሽ ባንክ ከአሥር ቢሊዮን ብር በላይ አዳዲስ ብድሮች የሰጠ ሲሆን፣ ይህም የ20 በመቶ ዕድገት በማስመዝገብ በሰኔ 2012 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ 56.8 ቢሊዮን ብር መድረሱ ታውቋል፡፡ በተቀማጭ ገንዘብ አሰባሰብ ረገድም ውጤት እንዳገኘም የሚያመለክተው የባንኩ መረጃ፣ በሒሳብ ዓመቱ አዳዲስ ቅርንጫፎችን ከፍቶ ለአገልግሎት ማብቃቱን አመልክቷል፡፡ ከ716,000 በላይ አዳዲስ ደንበኞች ወደ ባንኩ ማምጣት በመቻሉ ለባንኩ የተቀማጭ ገንዘብ ዕድገት አስተዋጽኦ አድርጓል ተብሏል፡፡ በቀዳሚው በጀት ዓመት ትልልቅ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችንና የግል ድርጅቶችን የባንኩ ደንበኞች ማድረግ መሆኑን፣ የባንኩ የኤቲኤም፣ የሞባይል ባንኪንግና የኢንተርኔት ባንኪንግ አዳዲስ ተጠቃሚዎችንም ለማፍራት በመቻሉም፣ የባንኩ ጠቅላላ የተቀማጭ ሒሳብ መጠን ከ73.6 ቢሊዮን በላይ መድረሱ ተገልጿል፡፡  የባንኩ የተቀማጭ ገንዘብ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ1.6 ቢሊዮን ብር ወይም የ19 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ተብሏል፡፡ ከተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች የሚያገኛቸው ገቢዎች በመጨመራቸው አዋሽ ባንክ የገቢ ምንጮቹን ለማስፋትና ለማሳደግ መቻሉን፣ ከዚህ መሠረት ከዲጂታል ባንኪንግ የአገልግሎት ዘርፍ፣ ከአገልግሎት ክፍያ፣ እንዲሁም ከመንግሥት የግምጃ ቤት ግዥና ከብሔራዊ ባንክ ቦንድ ግዥ የተገኙ ገቢዎች በአማካይ ከ30 በመቶ በላይ ጭማሪ ማሳየታቸው ተጠቁሟል፡፡ በአኃዛዊ መረጃው መሠረት ባለፈው ዓመት 7.9 ቢሊዮን ብር የነበረው የባንኩ ጠቅላላ ገቢ፣ በ2012 የሒሳብ ዓመት መጨረሻ ላይ 10.2 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡  ባንኩ ከግል ባንኮች ብልጫ ያሳየበት ነው የተባለለትን ጠቅላላ ሀብት በ15.93 ቢሊዮን ብር በማሳደግ 95.6 ቢሊዮን ብር ማድረሱ ታውቋል፡፡ ባለፈው ዓመት መጨረሻ  የባንኩ ጠቅላላ ሀብት 79.6 ቢሊዮን ብር ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስገዳጅ የቦንድ ግዥ መመርያን በማስቀረቱ፣ አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኢኮኖሚ ዘርፎች ከሚሰጠው ብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ እስከ 4.5 በመቶ የወለድ ቅናሽ ማድረጉ ይታወሳል፡፡በዓለም አቀፍ ደረጃና በኢትዮጵያም የተከሰተው የኮሮና ወረርሽኝ በኢኮኖሚው ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ ለመቀነስ፣ በተለይም በወረርሽኙ ክፉኛ የተጎዱትን የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም ለሆቴሎች ለአስጎብኝ ድርጅቶችና ለአበባ አምራቾች የወለድ ምጣኔ ወደ ሰባት በመቶ ዝቅ እንዲል ማድረጉ አይዘነጋም፡፡ አዋሽ ባንክ በ1987 ዓ.ም. ከደርግ ውድቀት በኋላ የመጀመርያው የግል ባንክ በመሆን ሥራ የጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተከፈለ ካፒታሉ 5.84 ቢሊዮን ሲደርስ፣ የቅርንጫፎቹ ብዛትም 466 ይታወቃል፡፡ ", "passage_id": "c44f1779c2ffecd8ab04d223c9dce8df" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 13.9 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡንና 27.2 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ የሀብቱን መጠን ከ380 ቢሊዮን ብር በላይ ለማድረስ መቻሉንም ገልጿል፡፡የ2008 በጀት ዓመት አፈጻጸሙን በማስመልከት ንግድ ባንክ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ መሠረት፣ ከሐምሌ 25 እስከ 30 ቀን 2008 ዓ.ም. ግምገማ ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ የባንኩን እንቅስቃሴ በቃኘው ግምገማ መሠረት በዓመቱ ከወጪ ንግድ፣ ከውጭ ከሚላክ ገንዘብና ከልዩ ልዩ ምንጮች 4.7 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል፡፡ ከውጭ ለሚገቡ ልዩ ልዩ ሸቀጦች ግዥ፣ ለነዳጅና ለሌሎች ግብዓቶች 6.8 ቢሊዮን ዶላር መክፈሉን ጠቁሟል፡፡ በመሆኑም ከሰበሰበው በላይ 2.1 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጉን የባንኩ መረጃ ይጠቁማል፡፡ በዓመቱ 46.8 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ በማሰባሰቡም የንግድ ባንክ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ከ288 ቢሊዮን ብር በላይ ማሻቀቡን አክሏል፡፡ ባለፈው ዓመት የነበረው ተቀማጭ ገንዘብ 241.7 ቢሊዮን ብር እንደነበር ያስታወቀው ባንኩ፣ በብድር የሰጠው አዲስ የገንዘብ መጠንም 92 ቢሊዮን ብር ገደማ መድረሱን ይፋ አድርጓል፡፡ ቀድሞ ከሰጣቸው ብድሮች መካከል 47.8 ቢሊዮን ብድር አስመልሻለሁ ብሏል፡፡በአሁኑ ወቅት 28‚467 ሠራተኞችን የሚያስተዳድረው ንግድ ባንክ፣ 2‚000 ያህል ሠራተኞችን ከቀድሞው ኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ መረከቡ አይዘነጋም፡፡ ይሁንና 1‚966 ያህሉ የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ከቀሪዎቹ የንግድ ባንክ ሠራተኞች ጋር በመቀላቀል እየሠሩ እንደሚገኙ ባንኩ አስታውቋል፡፡ ከተጠቀለለው ኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ከተረከባቸው ቅርንጫፎች መካከል 88 ቅርንጫፎች መደበኛ ሥራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ ብሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ 84 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈትም የባንኩ ጠቅላላ ቅርንጫፎች ቁጥር 1‚136 መድረሳቸውን ጠቅሷል፡፡በደንበኞች ረገድም በባንኩ ሒሳብ ያላቸው በጠቅላላው 13.3 ሚሊዮን እንደሆኑ፣2.8 ሚሊዮን ያህሉ የኤሌክትሮኒክ ባንክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች መሆናቸውን፣ ከዚህም በተጨማሪ በዓመቱ 600 ሺሕ የሚደርሱ ደንበኞች ለሞባይል ባንኪንግ እንዲሁም ከ24 ሺሕ በላይ ደግሞ ለኢንተርኔት ባንኪግ አገልግሎት መመዝገባቸው ታውቋል፡፡ በዚህም መሠረት ከ700 ሺሕ በላይ ደንበኞቹ የኢንተርኔት ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆናቸውንና ከ15 ሺሕ በላይ ደግሞ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት የሚያገኙ መሆናቸውን ገልጿል፡፡      ", "passage_id": "b11152ae985c7d5e5ccb307286030d82" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ መስከረም 21/2006 (ዋኢማ) – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የህብረተሰቡ የቁጠባ ባህል እንዲዳብርና የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ ለማሳደግ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።ባለፈው በጀት ዓመት የደንበኞች ቁጥር 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን፣ የተቀማጭ ገንዘብ መጠንን 154 ነጥብ 5 ቢሊዮን ማድረስ ተችሏል።ባንኩ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀው ‘’ ይቆጥቡ፣ይሸለሙ’’  ፕሮግራም ዛሬ በብሔራዊ ሎተሪ አዳራሽ 15 አውቶሞቢሎች፣ 15 ትራክተሮች፣ 15 እጣዎች እያንዳንዳቸው ለሁለት ሰዎች የአገር ውስጥ ጉብኝት ወጪ፣ 15 ብስክሌቶች፣ 15 የውሃ መሳቢያ ሞተሮችና 30 ላፕቶፖችን ጨምሮ በርካታ ዕጣዎች ወጥተዋል።የባንኩ የቢዝነስ ዴቬሎፕመንት ተወካይ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደተናገሩት ፕሮግራሙ ተግባራዊ በመደረጉ ባለፉት ሁለት ዙሮች በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በቁጠባ መልክ ከደንበኞች ተሰብስቧል፤ የደንበኞችንም ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ተችሏል።በሌላ በኩል ፕሮግራሙ ከዚህ ቀደም የባንክ ተጠቃሚ ያልሆኑ አያሌ ወገኖች ወደ ባንክ መጥተው የባንክ አገልግሎት ተቋዳሽ እንዲሆኑ ያስቻለ መሆኑን ገልፀዋል፡፡የሦስተኛውን ዙር ‘‘ይቆጥቡ፣ይሸለሙ’’ ፕሮግራም በቀጣይ ወራት በመተግበር ደንበኞቹን እያዝናና የቁጠባ ባህላቸውን ለማጎልበት እንዲቻል ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ተወካዩ ገልጸዋል።የባንኩን ተደራሽነት በማስፋት በየገጠር ከተሞች ጭምር በመዝለቅ ቅርንጫፎችን በመክፈት አጠቃላይ የቅርንጫፎችን ብዛት ከ700 በላይ በማድረስ ደንበኞች በቅርብ ርቀት አገልግሎቱን የሚያገኙበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።በቴክኖሎጂ ረገድም የኢንተግሬትድ ኮር ባንኪንግ ሶሉዩሽንስን ጨምሮ የተገበራቸው ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የሚሰጧቸው አገልግሎቶች በማቀላጠፍ ረገድ ትልቅ እገዛ እንዳላቸው አቶ ኤፍሬም ተናግረዋል።   (ኢዜአ)", "passage_id": "f5556bbed35fa6fbbe4a5bd50a6a2b6d" }, { "passage": "በበጀት ዓመቱ ሩብ ዓመት ጠቅላላ ሀብቱ 397.7 ቢሊዮን ብር መድረሱን የገለጸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ከታክስ በፊት አራት ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡ባንኩ ሪፖርቱ እ.ኤ.አ. ከጁላይ 1 ቀን 2016 እስከ ሴፕቴምበር 30 ቀን 2016 ድረስ የሩብ ዓመቱን የሥራ አፈጻጸም የሚዳስስ መሆኑን ገልጾ፣ እ.ኤ.አ. እስከ ኖቬምበር 18 ቀን 2016 ድረስ 1.2 ቢሊዮን ዶላር መሰብሰብ መቻሉን ጠቁሟል፡፡ ከወጪ ንግድ 209.1 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቱንና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ አገር ውስጥ ከተላከ የሐዋላ ገንዘብ 991.1 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቱን አክሏል፡፡የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሩብ ዓመቱ በብድርና በቦንድ ሽያጭ 17.7 ቢሊዮን ብር ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አቅርቦ 12 ቢሊዮን ብር ተመላሽ ማድረጉን ገልጿል፡፡ባንኩ በሩብ ዓመቱ ዋና ዋና ግቦችን ከማሳካት አኳያ ሰፊ ሥራዎችን ማከናወኑን አስታውቆ፣ ያገኘው ውጤት ለቀሪው በጀት ዓመት ዕቅድ አበረታች መሆኑን ጠቁሟል፡፡ በሩብ ዓመቱ 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈቱ ምክንያትም የቅርንጫፎቹን ብዛት 1,151 ማድረሱን የገለጸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የደንበኞቹም ቁጥር 13.9 ሚሊዮን መድረሱን አስታውቋል፡፡ 59 ቅርንጫፎቹን በመረጃ መረብ (ቲ-24 ኮር ባንኪንግ ሶሉዩሺንስ) ማገናኘቱንና በአጠቃላይ 1,115 ቅርንጫፎቹ በመረጃ መረብ መገናኘታቸውን ገልጿል፡፡የፖስ ማሽኖችን ቁጥር 6.092 ማድረሱንና የኤቲኤም አገልግሎቱን ወደ 1,065 ማድረሱን ጠቁሟል፡፡ 270,685 የባንክ ካርዶችን ለደንበኞቹ ማሠራጨቱንና የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎቹ 883,554 መድረሳቸውን ገልጿል፡፡ የኢንተርኔት ባንኪንግ ተጠቃሚዎችን ደግሞ 17,815 ለማድረስ መቻሉን በሩብ ዓመቱ ሪፖርት አስታውቋል፡፡", "passage_id": "f9f7f73e6dd386b68a72f2465becb827" } ]
dcd9a549464e4b810e8b34df1aa85f1f
e80eca1580a68f3b29b9aa3cc7463c5a
በመቀሌ ለነዋሪዎች ሰብዓዊ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ገለጸ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- መቀሌ ከተማ የደረሰው የእለት ደራሽ የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ ለዜጎች በመድረስ ላይ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ገለጸ። እንደ ኢዚአ ዘገባ፣ በመቀሌ ከተማ ለ80 ሺህ ዜጎች ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ እየተሠራ መሆኑን የጊዜያዊ አስተዳደሩ የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ ወይዘሮ ሳባ ገብረማርያም ገልጸዋል። የፌዴራል መንግሥት በክልሉ የምግብ፣ መድኃኒትና ሌሎች ቁሳቁሶችን በማቅረብ ላይ መሆኑን እና ጊዜያዊ አስተዳደሩም ለህዝቡ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝም ነው ያስረዱት።እንደ ወይዘሮ ሳባ ገለጻ፤ አሁን ላይ ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ እህል በመጋዘን ይገኛል። ይሄም እርዳታና ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች በመከፋፈል ላይ ነው። በዚህም በመቀሌ ከተማ ብቻ ለ80 ሺህ ዜጎች ድጋፉን ተደራሽ ለማድረግ እየተሠራ ነው። ሰብዓዊ ድጋፉ በመቀሌ ብቻ ሳይሆን በክልሉ የተለያዩ ከተሞችና ወረዳዎች በመዳረስ ላይም ይገኛል።በርካታ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎችም በችግር ላይ ያሉ ወገኖችን በመደገፍ ላሳዩት ተነሳሽነት ምስጋና ያቀረቡት ወይዘሮ ሳባ፤ ከፌዴራሉ መንግሥት የተላከውን ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገበት መድሃኒትም ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። ከፌዴራል መንግሥቱ በተጨማሪ ዓለም አቀፍ እና አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅቶችም ሰብዓዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ተናግ ረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37784
[ { "passage": "ቀይ መስቀል በትግራይ ክልል ወታደራዊ ግጭት ከተከሰተ ከአንድ ወር በኋላ የመጀመሪያውን የመድኃኒትና የእርዳታ አቅርቦት ወደ መቀለ ከተማ ማድረስ እንዳቻለ ገለጸ። ግጭቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ የግንኙነት መስመሮች በመቋረጣቸው ሳቢያ ለሳምንታት መድኃኒቶችና መሠረታዊ የህክምና አቅርቦት ተቋርጦ ነበር። በዚህም ምክንያት መደበኛ ሥራቸውን ለማከናወን ከባድ ችግር ውስጥ የነበሩትን የህክምና ተቋማት ለመደገፍ ከዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ እና ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የተላኩ መድኃኒቶች እና የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦቶች ዛሬ መቀለ ደርሰዋል። የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ባሰራጨው መግለጫ፤ በህክምና ተቋማት ውስጥ ያጋጠመውን ችግር ለመቅረፍ በሰባት ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች የተላከው ድጋፍ ግጭቱ ከተከሰተ በኋላ መቀለ ከተማ የደረሰ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ እርዳታ እንደሆነ አመልክቷል። በከተማዋ ላሉና ከከተማዋ ውጪ ለሚመጡ ህሙማን አገልግሎት የሚሰጠው የመቀለው አይደር ሪፈራል ሆስፒታል ግጭቱ ከተከሰተ በኋላ ባሉት ሳምንታት ውስጥ በነዳጅ እጦትና በመድኃኒቶች አቅርቦት መቋረጥ ምክንያት የጽኑ ህሙማንና የቀዶ ህክምና ክፍሎቹ አገልግሎት ለማቆም ተገደው እንደበር ተገልጿል። ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ እንዳለው፤ ሆስፒታሉ ከጥቅምት ወር መጨረሻ ጀምሮ በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸውን በርካታ ሰዎች ተቀብሎ የህክምና አገልግሎት ይሰጥ ነበር።ከዚህ በተጨማሪ የከፋ ህመም ላለባቸውና መደበኛ ክትትል ለሚፈልጉ የስኳር በሽተኞች፣ የኩላሊት እጥበት ለሚደረግላቸውና ለወላዶች አገልግሎት በመስጠት የሚታወቅ የጤና ተቋም ሲሆን፤ ሆስፒታሉ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሚገመቱ የከተማዋ ነዋሪዎች ዋነኛው የጤና ተቋም ነው።ከሳምንታት በፊት ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ባወጣው መግለጫ ከመድኃኒት፣ ከውሃ፣ ከኤሌክትሪክና ከሌሎች መሠረታዊ አቅርቦቶች አንጻር የአይደር ሪፈራል ሆስፒታል ያለበት ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን ጠቁሞ ነበር።ሆስፒታሉ በእጁ ላይ የነበረውን አቅርቦት በመጠቀም \"ለሳምንታት ያለ ተጨማሪ የመድኃኒት አቅርቦት፣ ያለ ውሃ እና መብራት በመቆየቱ ዶክተሮችና ነርሶች የትኞቹን አገልግሎቶች ትተው የትኞቹን እንደሚያስቀጥሉ ለመምረጥ በጣም ተቸግረው ነበር\" ሲሉ የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የአፍሪካ አህጉር ዳይሬክተር ፓትሪክ ዩሱፍ ተናግረዋል።ከአንድ ወር በኋላ ዛሬ ቅዳሜ ለሆስፒታሉ የደረሰው አቅርቦት ሆስፒታሉ ለሚያከናውነው የነፍስ አድን ሥራ ከማገዙም በተጨማሪ የህክምና ባለሙያዎቹ የነበረባቸውን ጫና እንደሚቀንስላቸው ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። በጣም አስፈላጊ የሆኑትን መሠረታዊ አቅርቦቶች ወደ መቀሌ በመላክ ከቀይ መስቀል በተጨማሪ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የበኩሉን እንዳበረከተ የተጠቀሰ ሲሆን፤ መድኃኒቶቹና እርዳታው በመቀለ ከተማ ከሚገኘው አይደር ሆስፒታል ባሻገር በክልሉ ጤና ቢሮ እና በቀይ መስቀል መድኃኒት ቤት አማካይነት ለአገልግሎት ይቀርባል ተብሏል። ዛሬ መቀለ ከተማ በቀይ መስቀል አማካይነት ከደረሰው የመድኃኒት አቅርቦት በተጨማሪ ብርድ ልብሶች፣ የፕላስቲክ መጠለያዎች፣ የማዕድ ቤት ቁሳቁሶች፣ አልባሳት እና ሳሙናዎች እንዲሁም የውሃ እና የንጽህና አገልግሎትን ለማግኘት የሚያስችሉ ቁሳቁሶች እንደደረሱ ተገልጿል። በጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ በፌደራል መንግሥቱ ሠራዊትና በህወሓት ኃይሎች መካከል የተቀሰቀሰውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ በትግራይ ክልለ ውስጥ የእንቅስቃሴና የግንኙነት መስመሮች በመቋረጣቸው ሳቢያ የህክምናና የሰብአዊ እርዳታ ተቋማት ለሳምንታት የመሠረታዊ አቅርቦቶች እጥረት አጋጥሟቸው ቆይቷል። የክልሉ ዋና ከተማ በፌደራል ሠራዊቱ ቁጥጥር ስር ከገባች በኋላ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ወደ ክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች እያቀረበ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።", "passage_id": "70d34e8c7d5d5a19884bdd3274971712" }, { "passage": "በትግራይ ክልል ወታደራዊ ግጭት ከተቀሰቀሰ ወዲህ በአካባቢው ሰብአዊ እርዳታ እየሰጠ ያለው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በስፍራው ከ50 በላይ የመጀመሪያ እርዳታ ሰጪ ቡድን ማሰማራቱን ለቢቢሲ ገልጿል።የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ እንግዳ ማንደፍሮ እንደተናገሩት፤ በአካባቢው ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ ድጋፍ እያደረጉ ሲሆን፤ ከ35 በላይ አምቡላንሶችን አሰማርተዋል።\"የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የትግራይ ቅርንጫፍ እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የአማራ ቅርንጫፍ አንድ ላይ የአምቡላንስ አገልግሎት፣ የመጀመሪያ ሕክምና እርዳታ አገልግሎትና ሌላም ድጋፍ እያደረጉ ነው\" ብለዋል።የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በአካባቢው ለሚገኙ ሆስፒታሎች ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶችን እየደጎመም መሆኑ ተገልጿል። \"ለተጎዱ ሰዎች የአምቡላንስ አገልግሎት ከመስጠት በተጨማሪ፤ በምዕራብ ትግራይ አካባቢ ለተፈናቀሉ ሰዎች ምግብ ነክ ያልሆኑ እንደ ብርድ ልብስ እና ፍራሽ ያሉ አስፈላጊ ቁሳቁሶችንም አከፋፍለዋል\" ብለዋል አቶ እንግዳ።የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ማኅበር ጋር በመሆን ለሆስፒታሎች የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ቁሳቁስ ከአምቡላንስ ጋር እንደሚደርስና ድጋፉ በሽረ፣ መቀለ፣ ወልድያ፣ ዳንሻ፣ ጎንደር እንደተዳረሰ አስረድተዋል። በግጭቱ ሳቢያ ጉዳት ስለደረሰባቸው ሰዎች ላቀረብንላቸው ጥያቄ፤ \"እስካሁን እያጓጓዝን ያለነው የተጎዱ ወታደሮችን ነው። ማይካድራ አካባቢ ጉዳት የደረሰባቸው ሰላማዊ ሰዎችን አጓጉዘናል። በሌላ አካባቢ ግን ሰላማዊ ሰዎች አላየንም\" ብለው መልስ ሰጥተዋል።ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ማኅበር በመቀለ አይደር ሆስፒታል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ቁሳቁሶች እንዲሁም የአስክሬን ማቆያ የፕላስቲክ ከረጢት እያለቀ መሆኑን ማስታወቁ ይታወሳል።ሆስፒታሉን የጎበኙ የድርጅቱ ባልደረቦች \"80 በመቶው ታካሚዎች በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸው ናቸው። ሌሎች ሕክምናዎች ቆመው ለድንገተኛ አደጋ ብቻ አገልግሎት እየተሰጠ ነው\" ብለዋል።የማኅበሩ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ኃላፊ ማሪያ ሶልዳድ \"ቁስል ለመስፋት የሚውል መገልገያ፣ ጸረ ተህዋሲ መድኃኒት፣ የህመም ማስታገሻ እና ሌሎችም መድኃኒቶች በአሳሳቢ ሁኔታ እያለቁ ነው\" ሲሉ ተናግረዋል።በግጭቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች ሕክምና በመስጠት ላይ ያሉ በአካባቢው የሚገኙ ሆስፒታሎች ውስጥ መጨናነቅ እንደሚፈጠር የገለጹት አቶ እንግዳ፤ ለሆስፒታሎቹ ድጋፍ እንዲደረግ አሳስበዋል።ይህ መጨናነቅ ቀደም ያለ ህመም ያለባቸው ሰዎች፣ ነፍሰ ጡር ሴቶች እና ሌሎችም ተገቢውን አገልግሎት እንዳያገኙ እንቅፋት መሆኑን አይቀርም።\"ሆስፒታሎቹ ከመደበኛው ውጪ ሥራ ሲኖራቸው ለሌሎች ህመምተኞች እገዛ ለማድረግ ይቸገሩ ይሆናል። ተጨማሪ ፍራሽ እና መድኃኒት የሚጠይቁትም ከመደበኛው ከፍ ያለ ሰው ስለገጠማቸው ነው። እኛም በደረስንባቸው አካባቢዎችም ይህን አስተውለናል። ሆስፒታሎቹ እና ጤና ተቋሞቹ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል\" ብለዋል።የተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ እርዳታ ሰጪዎች ለአካባቢው ማኅረበረሰብ ድጋፍ ለማድረግ መንገዶች ክፍት መደረግ አለባቸው ብለዋል።ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰብአዊ እርዳታ ሰጪዎች መንገድ እንደሚያመቻች መግለጹ አይዘነጋም።ከዚሁ ጋር በተያያዘ ድጋፍ ለማድረግ እንቅፋት ገጥሟቸው እንደሆነ የጠየቅናቸው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ እንግዳ \"ሠራተኞቻችን ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ቦታው ገብተው እየሠሩ ነው። አሁንም መስራት ቀጥለዋል። የደኅንነት ችግር አይኖርም አይባልም። እንደ ማንኛውም ድርጅት አንዳንድ ቦታዎች የደኅንነት ስጋቶች አሉን\" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።ከሦሰት ሳምንታት በላይ በትግራይ ክልል ውስጥ በፌደራል መንግሥቱ ሠራዊትና በህወሓት ኃይሎች መካከል የተካሄደው ወታደራዊ ግጭት ባለፈው ቅዳሜ የመቀለ ከተማ መያዝን ተከትሎ ዘመቻው ማብቃቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ማስታወቃቸው ይታወሳል። ግጭቱ ከተከሰተበት ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ጀምሮ በአካባቢው ያሉት የግንኙነት መስመሮች አስካሁን በመቋረጣቸው በጦርነቱ የሞቱ ሰዎችና የደረሰውን ጉዳት ለማወቅ አስተማማኝ መረጃ ማግኘት አዳጋች ሆኗል።ነገር ግን የተለያዩ የዕርዳታ ተቋማት በሦሰት ሳምንቱ ወታደራዊ ግጭት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወት ሳያልፍ እንዳልቀረ ይገምታሉ፤ ቀውሱን በመሸሽም ከ40 ሺህ በላይ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሸሻቸው ተነግሯል።የፌደራል መንግሥቱ መቀለን ከተቆጣጠሩ በኋላ በክልሉ ውስጥ መረጋጋትን በመፍጠር ጉዳት የደረሰባቸውን ለመርዳት እየሰራ መሆኑን ከመግለጹ በተጨማሪ ተፈናቅለው ወደ ጎረቤት አገር ሱዳን የገቡ ዜጎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደቀያቸው ተመልሰው እንዲቋቋሙ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር እየሰራ መሆኑን ገልጿል። ", "passage_id": "714764f572bc136b2d280e2852f0e743" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜናዊ የሀገራችን ክፍል የህግ ማስከበር ሂደት ከተጠናቀቀ ወዲህ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች እና የሕክም አቅርቦቶችን የያዘ የሰብዓዊ ድጋፍ በትግራይ ክልል ለሚገኙ 1ነጥብ 8 ሚሊየን ተጠቃሚዎች ደርሷል፡፡ነጥብ በክልሉ 2 5 ሚሊዮን ተጠቃሚዎችን ለማስተናገድ የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል፡፡በአስቸኳይ ጊዜ ማስተባበሪያ ማዕከል (ኢ.ሲ.ሲ) የሚኒስትሮች ኮሚቴ መሪነት አፋጣኝ ፍላጎቶችን ለማሟላት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ ከክልል ቢሮዎች፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅቶችና ከአለም ዓቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የተውጣጡ የቴክኒክ ቡድኖችን ያካተተ የአስቸኳይ ጊዜ ኦፕሬሽን ማስተባበሪያ ማዕከል (ኢ.ኦ.ሲ.) በመቀሌ ከተማ ተቋቁሟል፡፡ተጨማሪ ፍላጎቶችን ለመለየት ባለ አራት ደረጃ የአስቸኳይ ጊዜ ማስተባበር ሥርዓት (የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የምግብ ማከፋፈያ ቦታዎችን ያካተተ) ተደራጅቶ ወደ ስራ ተገብቷል፡፡ተለይተው ለታወቁ ተጠቃሚዎች የድጋፍ ሽፋንን ለማሳደግ እንዲሁም በፍጥነት አቅርቦትን ለማዳረስ የኢትዮጵያ መንግሥት ከልማትና ከሰብዓዊ አጋሮች ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ብሄራዊ የመከላከያ ሰራዊት ደህንነቱ የተጠበቀ የሰዎችና የአቅርቦቶች እንቅስቃሴን በማመቻቸት የሰብአዊ ዕርዳታውን ቅንጅት በከፍተኛ ደረጃ በመደገፍ ላይ ይገኛል፡፡ስርጭቱ በብሔራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፣ በአለም ዓቀፍ ሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ (ዩ.ኤን.ኦቻ) አስተባባሪነት በዓለም ዓቀፍና በሀገር በቀል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም በሴፍቲኔት መርሃ-ግብር (ፒ.ኤስ.ኤን.ፒ) እየተከናወነ ይገኛል።ስርጭቱ የሚከናወነው ከአክሱም፣ አዲግራት፣ አላማጣ፣ መቀሌ ዙሪያ፣ ሽሬ እና መቀሌ ከተማ ከሚገኙ የማሰራጫ ጣቢያዎች ነው፡፡በሂደቱ ለሴቶች፣ ሕፃናት፣ አረጋውያንና የአካል ጉዳተኞች ለምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁስና የሕክምና አቅርቦቶች ስርጭት ቅድሚያ እየተሰጠ ይገኛል፡፡መንግስት እና ሰብአዊ አጋሮች እ.ኤ.አ. ኖሼምበር 29 ቀን 2020 በተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት መሠረት በቅንጅት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ የተጠቃሚዎችን ብዛት በትክክል ለመለየት የጋራ የፍላጎት ዳሰሳና ግምገማ በማካሄድ ላይ ናቸው፡፡ለወገኖቻችን የሰብዓዊ ድጋፍ ለማዳረስ ትኩረት ተሰጥቶ በቁርጠኝነት ርብርብ እየተደረገ ይገኛል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!", "passage_id": "1777413e2475fd98368c710b16b1f94a" }, { "passage": "  - የመጀመሪያው 12 ሺህ ኩንታል የእርዳታ ስንዴ ደርሷል  - የተቋረጠው መብራት ትናንትና አገልግሎት ይጀምራል ተብሎ ነበር  - “ከጊዜያዊ የክልሉ አስተዳደር ጋር የማረጋጋት ስራ እየሰራን ነው” (ትዴፓ)   መቀሌ ወደ ቀድሞ ሰላማዊ እንቅስቃሴዋ እየተመለሰች መሆኑን የፈንቅል እና የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ትዴፓ) ሃላፊዎች ገለጹ።  ለትግራይ የሰብአዊ ድጋፍ እየቀረበ ሲሆን ከ16 ሚሊየን ብር በላይ የወጣበት የእርዳታ ስንዴና መድኃኒት ወደ ትግራይ እየተጓጓዘ ሲሆን ከነገ ጀምሮ መከፋፈል ይጀምራል ተብሏል። የመጀመሪያው ዙር 12 ሺህ ኩንታል የእርዳታ ስንዴ መቀሌ መግባቱም ተገልጿል።መንግስት ከጥቅምት 24 ምሽት ጀምሮ የህወሃትን አጥፊ ቡድን ለህግ ለማቅረብ የጀመረውን እርምጃ ተከትሎ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የዘለቀችው መቀሌ  በአሁኑ ሰዓት ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እየተመለሰች ነው ተብሏል። ህዝቡ ወደ ውጪ መውጣት ጀምሯል፤  ካፌዎች ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ ነው ሲሉ የፈንቅል ንቅናቄ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ይስሃቅ ወልዳይ በመቀሌ የሚገኝ አባላቸውን ጠቅሰው ነግረውናል።  አቶ ይሰሃቅ አክለውም  በቀጣይም ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ፣ የስልክና የባንክ አገልግሎት ይጀመራል መባሉን ተከትሎ ህዝቡ በደስታና በተስፋ መሞላቱን ገልጸዋል። ህዝቡ ከመከላከያ ሰራዊቱና ከጊዜያዊ የክልሉ አስተዳደር ጋር በመሆን የህወሃት የጦር መሳሪያ ማከማቻዎችን፣ የህወሃትን አላማ ለማሳካት ሲላላኩ የነበሩ ባንዳዎችንና ሌሎች የጥፋት ሴራዎችን እያጋለጠ እንደሚገኝ  ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል።ፈንቅል በቀጣይ በጦርነቱ ምክንያት ለችግር የተጋለጡትንና አስቸኳይ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን የክልሉን ነዋሪዎች ለመደገፍ የእርዳታ ድርጅቶችን አጋር በማድረግ እንደሚሰራ እና ከተማዋን የማረጋጋት ስራ ለመስራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል።የትዴፓ ሊቀመንበር አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ “ህወሃት አጥፍቶ ለመጥፋት የተነሳ የጥፋትና የጭካኔ ቡድን ነው ያሉ ሲሆን ጁንታው ቡድን ሁሉንም መሰረተ ልማቶች በማፈራረስና በማውደም የትግራይ ህዝብ በጨለማና በችግር እንዲኖር አድርጎት ቆይቷል ብለዋል። ህውሃት ህዝቡን ለ27 ዓመት ያፈነውና የተጨቆነው ሳያንስ አሁን በቅርቡም “ልትወረር ነው ልትወጋ ነው፤ ልታልቅ ነው” የሚል የባሰ ስጋትና ጭንቀት ውስጥ አስገብቶት የቆየ በመሆኑ አሁን በመከላከያ ሰራዊት መረጋጋት እያገኘ መሆኑን መቀሌ የሚገኙ አባሎቻችን ገልፀውልናል ብለዋል።  እንደ እርሳቸው ገለፃ፤ መብራት በመጥፋቱ ወፍጮ የሚባል ነገር አልነበረም፣ አሁንም መብራት፣ የባንክ አገልግሎት ስራ አልጀመረም፣ መድሃኒትም የለም። ሕዝቡ እነዚህን አገልግሎቶች ሳያገኝ በመቆየቱ በችግር ውስጥ በመሆኑ መንግስት እነዚህን መሰረተ ልማቶች በሌሎች የትግራይ አካባቢዎች ስራ እንዳስጀመረ ሁሉ በመቀሌም በፍጥነት ያስጀምራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን” ብለዋል።ሰሞኑን መቀሌ የደረሰውን የእርዳታ ስንዴም በተመለከተ የተሰራውን ስራ አድንቀው በሴፍትኔት ለሚኖረው አብዛኛው የትግራይ ህዝብም ሆነ ተሯሩጦና ያገኘውን ሰርቶ የእለት ጉርሱን ለሚያገኘው ሁሉ ከፍተኛ ችግር ሆኖ በመቆየቱ ተጨማሪ ድጋፍ ያስፈልጋል ያሉት ዶ/ር አረጋዊ፤ ፓርቲያቸው ከጊዜያዊው የክልሉ አስተዳደር ጋር በመተባበር የማረጋጋትና እርዳታ የሚያገኝበትን መንገድ በመፈለግ በኩል ከፍተኛ ስራ ይሰራል ብለዋል። ", "passage_id": "8264770a72ac46f542d46618bb7b04ec" }, { "passage": "በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፦ በሰሜናዊ የሀገራችን ክፍል የሕግ ማስከበር ሂደት ከተጠናቀቀ ወዲህ በትግራይ ክልል ለሚገኙ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎች የተለያዩ ሰብአዊ ድጋፎች መቅረባቸውን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ። መንግሥት ለወገኖቻችን የሰብዓዊ ድጋፍ ለማዳረስ ትኩረት ተሰጥቶ በቁርጠኝነት ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ትናንት ባወጣው መግለጫ፣ የሰብአዊ ድጋፉ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች እና የሕክምና አቅርቦቶችን መሆናቸውን አመልክቷል። በክልሉ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ተጠቃሚዎችን ለማስተናገድ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉንም ጠቁሟል። በአስቸኳይ ጊዜ ማስተባበሪያ ማዕከል (ኢ.ሲ.ሲ) የሚኒስትሮች ኮሚቴ መሪነት አፋጣኝ ፍላጎቶችን ለማሟላት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ ከክልል ቢሮዎች፣ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶችና ከዓለም ዓቀፍ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የተውጣጡ የቴክኒክ ቡድኖችን ያካተተ የአስቸኳይ ጊዜ ኦፕሬሽን ማስተባበሪያ ማዕከል (ኢ.ኦ.ሲ.) በመቀሌ ከተማ መቋቋሙን አስታውቋል ።ተጨማሪ ፍላጎቶችን ለመለየት ባለ አራት ደረጃ የአስቸኳይ ጊዜ ማስተባበር ሥርዓት (የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የምግብ ማከፋፈያ ቦታዎችን ያካተተ) ተደራጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል ብሏል።ተለይተው ለታወቁ ተጠቃሚዎች የድጋፍ ሽፋንን ለማሳደግ እንዲሁም በፍጥነት አቅርቦትን ለማዳረስ የኢትዮጵያ መንግሥት ከልማትና ከሰብዓዊ አጋሮች ጋር በቅንጅት በመሥራት ላይ እንደሚገኝ አመልክቶ፣ ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊት ደህንነቱ የተጠበቀ የሰዎችና የአቅርቦቶች እንቅስቃሴን በማመቻቸት የሰብአዊ ዕርዳታውን ቅንጅት በከፍተኛ ደረጃ በመደገፍ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።ሥርጭቱ በብሔራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፣ በዓለም ዓቀፍ ሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ (ዩ.ኤን.ኦቻ) አስተባባሪነት በዓለም ዓቀፍና በሀገር በቀል መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም በሴፍቲኔት መርሃ-ግብር (ፒ.ኤስ.ኤን.ፒ) እየተከናወነ ይገኛል። ሥርጭቱ የሚከናወነው ከአክሱም፣ አዲግራት፣ አላማጣ፣ መቀሌ ዙሪያ፣ ሽሬ እና መቀሌ ከተማ ከሚገኙ የማሠራጫ ጣቢያዎች ነውም ብሏል።በሂደቱ ለሴቶች፣ ሕፃናት፣ አረጋውያንና የአካል ጉዳተኞች ለምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁስና የሕክምና አቅርቦቶች ሥርጭት ቅድሚያ እየተሰጠ እንደሚገኝም፣ አስታውቋል።መንግሥት እና ሰብአዊ አጋሮች እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 29 ቀን 2020 በተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት መሠረት በቅንጅት እየሠሩ ይገኛሉ።የተጠቃሚዎችን ብዛት በትክክል ለመለየት የጋራ የፍላጎት ዳሰሳና ግምገማ በማካሄድ ላይ ናቸው።ለወገኖቻችን የሰብዓዊ ድጋፍ ለማዳረስ ትኩረት ተሰጥቶ በቁርጠኝነት ርብርብ እየተደረገ ይገኛል ብሏል።አዲስ ዘመን ጥር 12 ቀን 2013 ዓ.ም ", "passage_id": "bc421792c86e5fa44ec499fbb98f6884" } ]
b7a5c03bfd755b7197ad33ef944fbd83
51d70f649626a800c41661b9749822b9
የአንበጣ መንጋ ወደ ሰብል አብቃይ አካባቢዎች እንዳይዛመት እየተሠራ መሆኑን ተነገረ
ወርቅነሽ ደምሰውአዲስ አበባ፡- እንደ አገር በስፋት ተከስቶ የነበረውና አሁን ላይ በሱማሌ ክልል ብቻ ቀርቶ የነበረ የአንበጣ መንጋ ወደ ኦሮሚያና ደቡብ ክልል ሰብል አብቃይ አካባቢዎች እንዳይዛመት የመከላከል ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። በግብርና ሚኒስቴር የእጽዋት ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ በላይነህ ንጉሴ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በሱማሌ ክልል ላይ ብቻ ተወስኖ የነበረው የአንበጣ መንጋ አሁን ላይ ወደ ኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች በመስፋት ላይ ሲሆን፤ መንጋው ወደነዚሁ አካባቢዎች ሄዶ በደረሱ ሰብሎች ጉዳት እንዳያስከትል የኬሚካል ርጭት ተጠናክሮ እየተካሄደ ነው።እስካሁን በሱማሌ ክልል የነበረው የአንበጣ መንጋ በኩኩባነት ደረጃ ያለው ቢሆንም አሁን ላይ አድማሱን እያሰፋ በመብረር ላይ ስለሆነ በቀላሉ መዛመት የሚችል መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ ከታህሳስ ወር ጀምሮ በከፍተኛ ደረጃ ከሱማሊያ አካባቢ ያደገው የአንበጣ መንጋ በስፋት ወደ ሀገራችን እየገባ በመሆኑ፤ የመከላከል ሥራም በተጠናከረ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል። በሱማሌ ክልል የመከላከል ሥራ እየተሰራ ቢሆንም በመኪና ሆነ በሰው ኃይል በመግባት አንበጣውን መከላከል በማይቻልባቸው አካባቢዎች መንጋው በቀላሉ የመራባት ዕድል በማግኘቱ እና በሱማሌ ላንድና በፑትላንድ የሚደረገው የመከላከል ስራም እምብዛም በመሆኑ በቀጣይ በቂ መከላከል ካልተደረገ ሰብል አብቃይ ወደ ሆኑ አካባቢዎች በቀላሉ የመዛመት ዕድሉ አለ። እስካሁን 13 አውሮፕላኖች በመጠቀም የአሰሳ፣ የኬሚካል ርጭት ስራዎች እንዲሰሩ የተደረገ መሆኑን የሚናገሩት ዳይሬክተሩ፤ ባለፈው ከተከሰተው የአንበጣ መንጋ ዝግጅት አንጻር የአሁን ዝግጅት በኬሚካል አቅርቦትም ሆነ በርጭት ረገድ በቂ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። የዓለም ምግብ ድርጅት(ፋኦ) ኬሚካልንና አውሮፕላኖችን በማቅረብ ከፍተኛ እገዛ በማድረጉ ርጭቱ በሰፊው እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።አሁን ላይ በሱማሌ ክልል አምስት ዞኖች ላይ በጀረር፣ በዶሎ ፣ በሸበሌ፣ በቆራሄ ና በአፍዴር ያደገው አንበጣ በብዛት ጎልቶ የሚታይባቸው ቦታዎች በመሆናቸው ከፍተኛ ሁኔታ ርጭት እየተካሄደ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ከባሌ ሮቤ ላይ ተነስቶ ግኒርና ራይቱን ወደመሰሉ ቦታዎች፤ እንዲሁም በደቡብ በኦሮሚያና በሐመር አካባቢ ከአርባ ምንጭ በመነሳት ርጭት እየተካሄደ ይገኛል። አሁን ባለው ሁኔታ ቁጥጥሩ በተጠናከረ ሁኔታ እየተካሄደ ስለሆነ እስካሁን ከአቅም በላይ የሆነ የአንበጣ መንጋ የለም ብለዋል ።ከፌዴራል ጀምሮ ከክልሎች አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጋር የተዘረጋው ቅንጅታዊ አሰራር ውጤት እያመጣ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ በተለይ አርሶ አደሩ አንበጣ ያለበትን መረጃዎች በመስጠትና በህብረት በመስራት የሚያደርገው ጥረት መንጋውንለመከላከል እንዳስቻለ አመልክተዋል።እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ በሱማሌ ላንድ ላይ የአንበጣ መንጋን ለመከላከል እየተደረገ ያለው ጥረት አመርቂ ባለመሆኑ መንጋው በከፍተኛ ደረጃ ወደ ኢትዮጵያ ይገባል የሚል ስጋት ያለ ሲሆን፤ በዚህ በኩል የሚገባ ከሆነ ደግሞ ከዚህ በተሻለ ተጠናክሮ ካልተሰራ የንፋሱን አቅጣጫ ተከትሎ ወደ ደቡብ ሄዶ የመስፋፋት ሁኔታ ይኖራል። ምንም እንኳን ከሱማሌ ላንድ በኩል የሚመጣው የመንጋ መጠን ከፍተኛ እንደሚሆን ቢገመትም ኢትዮጵያ የመከላከል አቅሟን በማሳደጓና በቂ ቅድመ ዘግጅት በማድረጓ መንጋው ወደ ሀገር ውስጥ ቢገባም ከቁጥጥር ውጪ ይሆናል የሚል ግምት እንዳሌለ ያብራራሉ።የአንበጣ መንጋው ርጭቱ እየተካሄደ ያለው በቆላማ በሱማሌ ክልል አካባቢ ሲሆን፤ በሳር ላይና በግጦሽ ላይ ጉዳት እያደረሰ ቢሆንም እስካሁን ባለው ሁኔታ አካባቢ ላይ ሰብል ባለመኖሩ ጉዳትአልደረስም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ወደፊት የመስኖ ሰብሎች እየተመረቱ ያሉ ሲሆን፤ በተለይ ወደ ጎዴና ኦሮሚያ ውስጥ ራይቱ አካባቢ አሁን ላይ ሰብሎች በመዝራታቸው በተለይ ከቆላ ስንዴ ጋር ተያይዞ እየለሙ ያለበት ሁኔታ በመኖሩ በተቻለ አቅም ትኩረት በማድረግ እዚያ አካባቢ ሊያርፍ የሚችለውን የአንበጣ መንጋን ለመከላከል ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ አቶ በላይነህ ጠቁመዋል።በቀጣይም በፌዴራል፣ በክልሎችና መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች በኩል የተቀናጀ አሠራር በመዘርጋት መንጋው ጉዳት እንዳያስከትል የተናበበ ሥራ እንደሚሰራ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ መንጋው በመስኖ የሚለሙ ቦታዎች ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመዋል። በድንበር በኩል ገብቶ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትልም ከሶማሊያና ከኬኒያ መንግሥታት ጋር የተናበበ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37794
[ { "passage": "በምሥራቃዊ የአማራ አካባቢዎች የተከሰተው የበርሃ አምበጣ መንጋ እየቀነሰ ቢመጣም አሁንም የመከላከል ሂደቱ ተጠናክሮ ካልቀጠለ የሚያስከትለው ጉዳት የከፋ ሊሆን ይችላል ተባለ፡፡የአምበጣ መንጋው በክረምት ወቅትና በደጋማ አካባቢዎች መከሰቱ ያልተለመደ እንደሆነ የኮምቦልቻ እፅዋት ጥበቃ ክሊኒክ አስታቋል፡፡ መኸር የህልውናው መሰረት ለሆነው የምሥራቃዊው የአማራ አርሶ አደር እየጣለ ያለው የክረምት ዝናብ ሁለት ዓይነት ስሜት ፈጥሮበታል - ተስፋና ስጋት፡፡የዝናቡ ስርጭት አለመቀነስ ተስፋውን ሲያለመልመው ባልተለመደ ሁኔታ በዝናብና በደጋማ አካባቢዎች የበርሃ አምበጣ መንጋ መከሰቱ ለፍርሃት ዳርጎታል፡፡።\n", "passage_id": "c31877c3e8a27c5ceb1816a1528c8da0" }, { "passage": "በአፋር ፣ ሶማሌ፣ ትግራይ ፣ እና አማራ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ የተወሰኑ ስፍራዎች የበረሃ አንበጣ መንጋ መታየቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ከአሁን በፊት ለ30 ያክል ጊዜያት ከተለያዩ የአረብ እና አፍሪቃ ቀንድ ሀገራት ተነስቶ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት የገባን ሰብል አጥፊ የአንበጣ መንጋ በአውሮፕላን በታጀበ ርብርብ ማስወገዱን ያስታወሱት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የዕፅዋት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘብዴዎስ ሰላቶ ፣አሁን የተሰከሰተውን እና በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ይገባል ተብሎ የሚጠበቀውን ፤ ሌላ የወጣት አንበጣ መንጋ በተመሳሳይ ለመከላከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ተናግረዋል፡፡አቶ ዘብዲዎስ ጋር ያደረጉትን ሙሉ ቆይታ ያዳምጡ፡፡ ", "passage_id": "3558a0421489b6984471da7e7fbd0758" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ መስከረም 28/2013ዓ.ም (አብመድ) የበርሃ አንበጣ መንጋ በምሥራቅ አማራ አካባቢዎች ከተከሰተ ቆይቷል፡፡ መንጋው ከተከሰተበት መስከረም 6/2013 ዓ.ም ጀምሮ በየአካባቢው የሚገኙ አርሶ አደሮች፣ የግብርና ባለሙያዎች እና በየደረጃው ያሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ስርጭቱን ለመቆጣጠር ባህላዊ እና ዘመናዊ መንገዶችን እየተጠቀሙ ቢሆንም በበርካታ አካባቢዎች ከቁጥጥር ውጭ እየሆነ መምጣቱን ተመልክተናል፡፡ዛሬ በጠዋት በተገኘንበት በሰሜን ወሎ ዞን ሐብሩ ወረዳ ቀበሌ 27 አካባቢ በጠዋት በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት ሲካሄድ አርፍዷል፡፡ ነገር ግን በአካባቢው መልካ ምድራዊ አቀማመጥ እና ሰው በሚኖርባቸው ቦታዎች ለርጭት ምቹ ያልሆኑ አካባቢዎች ላይ መንጋው ሰፍሮ በሰብል ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው፡፡በሐብሩ ወረዳ በ13 ቀበሌዎች የአንበጣ መንጋው ተከስቷል፤ በሦስት ቀበሌዎች ላይ ያለ ሰብል ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ ሆኗል፡፡", "passage_id": "9897efa19f9ca18ae840f3608beccb42" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የተከሰተው የበረሃ አንበጣ መንጋ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ ተገለፀ።በምስራቅ አማራ ሰሜን እና ደቡብ ወሎ ዞኖች የተከሰተው የአንበጣ መንጋው በሰብል ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ ተነግሯል።በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ የተከሰተው መንጋ የጉዳት መጠኑ ከፍተኛ መሆኑን የወረዳው አርሶ አደሮች ተናግረዋል፡፡በወረዳው የተከሰተው የበረሃ አንበጣ መንጋ 24 ሺህ ሄክታር የሚሆን መሬት የወረረ መሆኑን የገለጸው የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ ‘‘በወረዳው በ11 ቀበሌዎች ይገኝ የነበረ ሰብል ላይ ከ10 እስከ 100 በመቶ ጉዳት አድርሷል’’ ብሏል፡፡አንበጣ መንጋውን ለመከላከል ሕዝቡን በማስተባበር እና አሮጌ የመኪና ጎማዎችን ከከተማ በማስመጣት ጭስ እያጨሱ በባህላዊ መንገድ ለመከላከል ጥረት እየተደረገ መሆኑን አብመድ ዘግቧል።የመንጋው ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመምጣቱ የመከላከል ሥራው ውጤታማ እንዳልሆነም ገልጸዋል፡፡በተመሳሳይ የአንበጣ መንጋው  በትግራይ ክልል ደቡባዊ ትግራይ ዞን ሶስት ወረዳዎች ማለትም ራያ አዘቦ ፣ ራያ አላማጣ ፣ ራያ ጨርጨር ተከስቷል።በዞኑ የተከሰተውን የአንበጣ መንጋ በባህላዊ መንገድ ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥረት እያደረገ ይገኛል።በዚህም ወጣቶች፣ የመንግስት ሰራተኞች የፀጥታ አካላት፣ የተለያዩ የእግር ኳስ ቡድን ደጋፊዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ከፍሎች አንበጣውን የመከላከል ስራ እያከናወኑ ነው።", "passage_id": "ef0d6be351d82d3737234d1064bf2c3b" }, { "passage": "መንጋውን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት ቢቀጥልም ተጨማሪ የኬሚካል ርጭት የሚያደርግ አውሮፕላን ያስፈልጋልም ተብሏል፡፡ባሕር ዳር፡ መስከረም 27/2013ዓ.ም (አብመድ) በምሥራቅ አማራ የተከሰተው የበረሃ አንበጣ መንጋ በተለያዩ አካባቢዎች ጉዳት እያደረሰ ሲሆን በወረባቦ ወረዳ የተከሰተው መንጋ ግን የጉዳት መጠኑ ከፍተኛ መሆኑን የወረዳው አርሶ አደሮች ተናግረዋል፡፡‘‘በተለያዩ ባህላዊ መንገዶች ስንከላከል ቆይተናል’’ ያሉት አርሶ አደሮቹ አሁን ላይ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ እጃቸውን አጣጥፈው አልተቀመጡም፤ የሚመለከተው አካል በተለይ የክልል ግብርና ቢሮና የፌዴራል ግብርና ሚንስቴር ግን የመከላከል ሥራውን በበቂ መጠን እየሠሩ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡በወረባቦ ወረዳ የተከሰተው የበረሃ አንበጣ መንጋ 24 ሺህ ሄክታር የሚሆን መሬት የወረረ መሆኑን የገለጸው የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ ‘‘በወረዳው በ11 ወረዳዎች ይገኝ የነበረ ሰብል ላይ ከ10 እስከ 100 በመቶ ጉዳት አድርሷል’’ ብሏል፡፡በመንጋውም ከ3 ሺህ 400 በላይ አርሶ አደሮች ሰብላቸው ሙሉ በሙሉና በከፊል እንደወደመባቸው የገለጹት የመምሪያው ኃላፊ ታደሰ ግርማ የበረሃ አንበጣ መንጋውን ለመከላከል ሕዝቡን በማስተባበር እና አሮጌ የመኪና ጎማዎችን ከከተማ በማስመጣት ጪስ እያጨሱ በባህላዊ መንገድ ለመከላከል ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የመንጋው ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመምጣቱ የመከላከል ሥራው ውጤታማ እንዳልሆነም ገልጸዋል፡፡በስፍራው የበረሃ አንበጣ መንጋ ለመከላከል የኬሚካል ርጭት ስታደርግ የነበረችው ሄሊኮፕተር ከሰሞኑ መከስከሷ መንጋውን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት መፍጠሩንም አመልክተዋል፡፡ የፌዴራል መንግሥት ተጨማሪ የኬሚካል ርጭት የሚያደርጉ አውሮፕላኖችን ወደ ስፍራው እንዲያሰማራም ጥሪ አቅርበዋል፡፡", "passage_id": "e89dc5595a8043d13ed110c7d389b0a6" } ]
86dd0cf6e79470e4f77e7c308457a912
3edfb11170db1ab0425775c58b94743f
በህግ ማስከበር ዘመቻው ግዳጃቸውን በጀግንነት ለፈጸሙ የሰራዊቱ አባላት እውቅና እንደሚሰጥ ተገለጸ
– የክልሎች አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል ሃይማኖት ከበደአዲስ አበባ:- በትግራይ ክልል በተደረገው የህግ ማስከበር ዘመቻ ግዳጃቸውን በጀግንነት ለፈጸሙ የሰራዊቱ አባላት በየደረጃው እውቅና እንደሚሰጥ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የክልል ልዩ ሃይሎች በየቦታው የነበራቸው አስተዋጽ ከፍተኛ መሆኑንም አስታውቀዋል። ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ትናንት ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ላይ እንዳስታወቁት፤ በዚህ የህግ ማስከበር ላይ የተሳተፉ የሰራዊቱ አባላት እንደየደረጃቸው የተለያዩ ሽልማቶችን የሚሸለሙ ይሆናል። ሜዳሊያ እና ማዕረግ የሚሸለሙ እንዲሁም ሌሎች የዕውቅና አሰጣጥ ሥነ ስርአቶችም የሚሰጡ ይሆናል።“ጀግኖች ይሸለማሉ ታሪካቸውም ተፅፎ ለትውልድ ይቀመጣል” ያሉት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ፤ እነዚህ ጀግኖች የሀገር ቅርስ ስለሆኑ እነሱን ማስተዋወቅ፣ መጠበቅና ማበረታታት ተገቢ ነው ሲሉም አስታውቀዋል።እንደ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ማብራሪያ፤ በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ የህዝቡ ተሳትፎ ከፍተኛ የነበረ ሲሆን፤ የአማራ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና ሌሎችም ክልሎች በተለያዩ መንገዶች ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደነበር አብራርተዋል።የቆሰሉ የሰራዊቱ አባላት በአብዛኛው በአማራ ክልል ሆስፒታሎች ሲታከሙ መቆየታቸውን የገለጹት ጄኔራል ብርሃኑ፤ በክልሉ ያሉ ሆስፒታሎችና የህክምና መስጫ ተቋማት ለሰራዊቱ ክፍት እንዲሆኑ በማድረግ አምቡላንስና የህክምና ባለሙያ መድበው ቁስለኞችን በሰፊው ማከማቸውንና ሪፈር የተባሉት ብቻ ወደማዕከል መምጣታቸውን አስታውቀዋል። “ጁንታው በውጊያ ሲወጠር ባዶ እጃቸውን አግኝቷቸው ሳይማርክ ማርኬያለሁ ብሎ የፎከረባቸውና የታገቱ አባሎቻችንን ጥሏቸው ሲጠፋ ወደአማራ ክልል ነው የመጡት፤ አማራ ክልል ከድንበሩ ጀምሮ እስከመጨረሻው የመሰባሰቢያ ወረዳ ድረስ አጓጉዞ፣ አብልቶ፣ ሞራል ሰጥቶ ወገናዊነቱን አሳይቶ ነው የሸኛቸው፤ ይህ በጣም ከባድ ስራ ነው” ሲሉም ነው የክልሉ ህዝብን አስተዋጽኦ የገለጹት።“እኛ ያደረግነው እነሱ ያሰባሰቡትን፣ ያደራጁትንና በዩኒቨርሲቲ ያቆዩትንና የመገቡትን ተቀብለን ኦረንቴሽን ሰጥተን ነው ወደክፍላቸው የመለስናቸው” ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ “እኛ የጁንታውን ዋና ሃይል እየመታን ስንሄድ በእያንዳንዱ ውጊያ የአማራ ክልል ልዩ ሃይል ብዙ ቀዳዳ ሸፍኗል፤ ውጊያ ያለበት እየተዋጋ ውጊያ የሌለበት ደግሞ ቀጣናውን በመሸፈን ሰራዊቱ ቀጣና እሸፍናለሁ ብሎ ሃይል እየቀነሰ እንዳይሄድ አድርጓል፤” ሲሉም ነው የተናገሩት።እንደ ጄኔራል ብርሃኑ ገለጻ፤ በኦሮሚያም በኩል የነበረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው። ከክልሉ ፕሬዚዳንት እና ከተወሰኑ አመራሮች በስተቀር ሁሉም አመራር ወደወረዳ አስገብቶ ልዩ ሃይሉን አስገብቶ በሸኔ በኩል ታቅዶ የነበረው እድል እንዳያገኝ የማድረግ ስራ ተሰርቷል። ሶማሌ ክልልም ራሱን ችሎ ጸጥታውን በመቆጣጠር ምንም ኮሽታ ሳይሰማ የህግ ማስከበር ዘመቻው መጠናቀቁን የገለጹት ጄነራል ብርሃኑ፤ በክልሉ በምስራቅ ዕዝ የሚጠበቁ ብዙ ተቋማት እንደነበሩና አልሸባብም በዚያ አካባቢ የሚንቀሳቀስ ቢሆንም ሁሉንም ስራ የክልሉ መንግስት ልዩ ሃይል በራሱ እንዳከናወነ አብራርተዋል። በተመሳሳይም የአፋር ክልል ልዩ ሃይል ያደረገው አስተዋጽኦ ላቅ ያለ መሆኑን የገለጹት ጄኔራል ብርሃኑ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ህዝብም በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ገንዘብ አዋጥቶ ለሰራዊቱ ማበርከቱን በመጥቀስ መላው የአገሪቷ ህዝብ በተለያየ አስተዋጽኦ የተሳተፈበት ዘመቻ በድል መቋጨቱን አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37843
[ { "passage": "አስቴር ኤልያስአዲስ አበባ፡- መከላከያ ሰራዊታችን በሶስት ሳምንት ውስጥ በታላቅ ጀብዱ የኢትዮጵያዊነታችንን ልክ እንዳሳየን የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የዓለም አቀፍና ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ አስታወቁ ፡፡ዶክተር ቢቂላ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት\nቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት\n፤ በትግራይ ክልል ተሸሽጎ የከረመው\nጽንፈኛው የህወሓት ስግብግቡ\nጁንታ በአገር   መከላከያ ሰራዊት\nላይ የፈጸመውን ጥቃት\nተከትሎ መንግስት የሕግ\nማስከበሩን ተግባር ባከናወነበት\nወቅት የአገር መከላከያ\nሰራዊት ትልቅ ጀብድ\nበመፈጸም የኢትዮጵያዊነትን ልክ\nአሳይቶናል ።መከላከያ ሰራዊቱ\nበሶስት ሳምንት ውስጥ በሰራው ጀብዱ በእርግጥም ታላቅነቱንም አስመስክሯል ፡፡ መከላከያ ሰራዊቱ፤ ‹በአገሬ ከመጣህማ እኔን ታርዳለህ እንጂ ትጥቄን አትፈታም፤ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና በአገሬ ማንነት ከመጣህ ትጨርሰኛለህ እንጂ በዘር አትከፋፍለንም የሚል የጀግንነት ጥግ አሳይቷል “ ያሉት ዶክተር ቢቂላ ፤ በተለይም ውስጥ ያሉ አመራሮች ትጥቃቸውን ፈተው ላለመስጠት ያደረጉት ተጋድሎ ታላቅ ነው ብለዋል።ሌላ ኃይል እስኪደርስላቸው ድረስ አንገት ለአንገት ተናንቀው የታገሉ መሆናቸውንም አስታውቀዋል ። ከድሉ ጀርባ ያለው የአገር አንድነት መለከያ ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን እንደሆነም ጠቁመዋል ። እንደ ዶክተር ቢቂላ ገለጻ፤ በዚህም ብቻም ሳይሆን ወደ ፊትም ትልልቅ አገራዊ ፈተናዎች ቢከሰቱ እንኳ መከላከያ ሰራዊቱ ያልቃታል እንጂ አገሩን እንደማያስደፍር ማረጋገጥ ተችሏል።ይህን ጀግንነቱንም በማየት ከኋላው 115 ሚሊዮን ሕዝብ ተገልብጦ ኢትዮጵያ ተነካች በማለት ለመከላከያው ያለውን ድጋፍ ገልጿል፡፡ የአገር መከላከያ ሰራዊትን ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከዳር መጥተው ያቋቋሙትና ከየትኛው ብሔርና ኃይማኖት ነህ ሳይል አብሮ የሚኖር የኢትዮጵያዊነት መገለጫ ነው ያሉት ዶክተር ቢቂላ፣ ጁንታው ፤ ዜጎች እንደ አይናቸው ብሌን የሚያዩዋትን ኢትዮጵያን ለማጠልሸት ፤ የኢትዮጵያዊነት መገለጫ፣ የአገራዊ አንድነት ምልክት በሆነው መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት መሰንዘሩን አመልክተዋል ፡፡ ከኢትዮጵያዊነት መገለጫዎች አንዱ መከላከያ ሰራዊታችን ነው ያሉት ኃላፊው ፣ በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የማይታይ ኢትዮጵያ የለም ያሉት ዶክተር ቢቂላ፣ ይህንን ሰራዊት በዘር ለይተው ማጥቃታቸውንም አመልክተዋል።ይህም የተንኮልና የክፋት ሥራቸው ለታሪክ የሚቀመጥ ነው ብለዋል፡፡ ዩኒቨርስቲን፣ ፌዴራል መንግስትን፣ መከላከያን መንካት ኢትዮጵያ መንካት ነው። የአይንን ብሌን መንካት እንደሆነ ያመለከቱት ዶክተር ቢቂላ፣ ከዚህ ድል ጀርባ ያለውን መከላከያ መንካት ማለት የኢትዮጵያውያን አንድነትና መስተጋብርን መንካት እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ ከዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ ሙሉ ቃል ገጽ 6 ይመልከቱ ፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 29/2012 ዓ.ም ", "passage_id": "290aaa7572dc3025c6077041f3700371" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከመከላከያ በተለያዩ ምክንያቶች በክብር የተሰናበቱና የ20ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አባላት የነበሩ ወታደሮች እና የመከላከያ የእግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾች “ደማችን ለጀግናችን” በሚል መሪ ቃል ደም ለግሰዋል፡፡በሰሜን ዕዝ የሰራዊት አባላት ላይ በህገ ወጡ የህወሓት ቡድን የተፈፀመው ክህደት ተግባር እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል፡፡አባላቱ “ጦርነትን የማይናፍቀው ግን ደግሞ ጦርነት ሲገጥመው እንደ አራስ ነብር አስፈሪነቱን በተግባር የሚያሳየው ሰራዊታችን ህግን የማስከበርና የህልውና ዘመቻ ላይ ባለበት ወቅት ደም በመለገሳችን ኩራት ይሰማናል” ብለዋል፡፡በሠራዊቱ ላይ ጥቃት የፈፀመው የህወሃት ቡድን ተደምስሶ ለፍርድ እስኪቀርብ ድረስ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በጋራ እንቆማለን ሲሉም ተናግረዋል።የእናት ጡት ነካሹ የህውሓት ቡድን በሰሜን ዕዝ ሠራዊታችን ላይ የፈፀመው ክህደት እና ጥቃት እጅግ አስቆጥቶናል በመሆኑም በማንኛውም መልኩ ከሠራዊታችን ጎን ቆመን መስዋዕትንት ለመክፈል ዝግጁ ነን ብለዋል።እንዲሁም የመከላከያ የእግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾችና አሰልጣኞችም ለመከላከያ ሰራዊቱ ያላቸውን አጋርነት ለማሳየት ደም ለግሰዋል።የእግር ኳስ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አቶ ዮሀንስ ሳህሌ የህወሓት ሕንፈኛ ቡድን ሀገርን በሚያገለግለው ሰራዊት ላይ ጥቃትና ክህደት በመፈፀሙ ማዘናቸውን ተናግረዋል።በሌላ ዜና አቶ ዳዊት ሀይለማሪያም የተባሉ ግለሰብ 18 ሺህ 800 የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ለሀገር መከላከያ ሰራዊት መለገሳቸው ተገልጻል።አቶ ዳዊት እንደተናገሩት መከላከያ ማለት ሀገር ማለት ስለሆነ በዚህ ወቅት ከጎንህ ነን ለማለት ነው ድጋፉን ያደረግነው ብለዋል።ድጋፉን የተረከቡት ሜጀር ጄነራል ታደሰ መኩሪያ በበኩላቸው፥ ሠራዊቱ በህግ ማስከበር ግዳጅ ላይ እያለ ይህንን ድጋፍ በማበርከታቸው ትልቅ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ስጦታውም ለብሔራዊ ድጋፍ አስባሳቢ ኮሚቴ ገቢ እንደሚደረግ መናገራቸውን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።", "passage_id": "122e64b52c685867dcc3d793b7db2572" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ታህሳስ 4 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል ያሰለጠናቸውን የ33ኛ ዙር መሠረታዊ የኮማንዶ ሰልጣኞችን አስመርቋል ።ተመራቂዎቹ ሁለት ሻለቃ ሲሆኑ መደበኛ እና መደበኛ ያልሆኑ ግዳጆችን በብቃት መወጣት የሚያስችል ክህሎች መጨበጣቸው ተገልጿል።የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ሹማ አብደታ ባደረጉት ንግግር ÷ የክፍላችን የሠራዊት አባላት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተካሄደው ዘመቻ የሰሯቸው ገድሎች አንፀባራቂ ናቸው ብለዋል ።አያይዘውም በወታደራዊ ሳይንስ የተካኑት የልዩ ዘመቻዎች ሀይል አባላት ፣ ጁንታው የሚመካበትን ምሽግና የታጣቂ ሀይል ስብስብ በመደምሰስ ለወገናቸው ድል አብስረዋል ነው ያሉት።የዛሬ ተመራቂዎችም የክፍላችሁን አንፀባራቂ ታሪክ ለመጠበቅ ፣ በቅብብሎሽ ወደር የሌለው ጀግንነትን መፈፀም እንደምትችሉ አልጠራጠርምም ነው ያሉት ።ታሪክ በመስራት የታሪኩ ባለቤት ለመሆን እነሆ በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሳችኋልም ሲሉ ገልጸዋል ።የማሰልጠኛ ማዕከሉ ዋና አዛዥ ተወካይ ኮሎኔል ተዝገራ ከበደ በበኩላቸው ÷ ተመራቂዎች ፣ ተኩስን በመጠቀም የተለያዩ የመሬት ገፆች ፣ በቀንና በሌሊት የሚጠይቁትን ስልታዊ እንቅስቃሴዎችን የማድረግ ፣ መደበኛ የሆኑና ያልሆኑ ግዳጆችን ከጠላት ፊትና ጀርባ መፈፀም የሚ ያስችል አቅም ፈጥረዋል ማለታቸውንከኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!", "passage_id": "7853f341e768559b87bdf52257158004" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የመከላከያ ሰራዊት በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የሚመጣ ውጫዊም ሆነ ውስጣዊ ኃይልን ለመመከት ዝግጁ መሆኑን የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሹማ አብደታ ተናገሩ።ሰራዊቱ በማንኛውም የሀገሪቱ ክፍሎች ተንቀሳቅሶ ሀገርንና ህዝብን የመጠበቅ ህገ-መንግስታዊ ስልጣኑን የሚያስቆመው አካል እንደሌለም ገልጿል።በሀገር መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ሹማ አብደታ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ቆይታ አድርገዋል።ሰራዊቱ በአሁኑ ወቅት ከስነ-ምግባር ጀምሮ የቴክኒክ፣ የትጥቅ፣ የአቅምና ሌሎች አጋዥ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በሚገባ መጠቀም የሚችል፣ በማንኛውም ስፍራ ፈጥኖ ደርሶ ተልዕኮውን መወጣትና ማንኛውንም ጠላት መመከት የሚችልበት ጠንካራ ቁመና ላይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።በተለይም በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ግድቡ ከመጀመሩም ሆነ ውሃ ከመሞላቱ በፊት የተለያዩ ማስፈራሪያዎች ይሰነዘሩ እንደነበርና ሰራዊቱ ይህንን በመገንዘብ ምንጊዜም በተጠንቀቅ የቆመ ነው ብለዋል።የልዩ ዘመቻዎች ኃይል በልዩ ኮማንዶ፣ በባህር ጠላቂ ሃይል፣ በአየር ወለድና መሰል አደረጃጀቶች የተደራጀና ማንኛውም ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ መሰናክል ሳይወስነው ግዳጁን የሚወጣ ነው ሲሉ ተናግረዋል።ከዚህ በተጨማሪም ሰራዊቱ በተለይ አሁን ካላው የፖለቲካ ሁኔታም ይሁን የተፈጥሮ አደጋዎች ጋር ተያይዞ የሀገርን ሰላም፣ የሰው ህይወትና ንብረት ለመጠበቅ በሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫዎች ተንቀሳቅሶ ይሰራል ብለዋል።” የፖለቲካ ጉዳይ የፖለቲከኞች ነው “ያሉት ሜጀር ጀኔራሉ ሰራዊቱ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ ስራውን ለመስራት የሚያስቆመው አካል የለም ሲሉ ተናግረዋል።“የመከላከያ ሰራዊት የአንድ ክልል ወይም የግለሰብ አይደለም” ያሉት ዋና አዛዡ ዓላማው የአገር ህልውና እንዲቀጥል፣ ህዝቦች በሰላም ወጥተው እንዲገቡ ማድረግ እስከሆነ ድረስ ሁሉም የኔ ነው ብሎ መደገፍና ከጎኑ መቆም አለበት ብለዋል።ፖለቲካዊ ጉዳዮች ውስጥ መከላከያ እንደማይገባ አስታውሰው ከዚህ ያለፈ ችግር ሲኖር ግን መከላከያ ቁንጮና የመጨረሻው መፍትሄ ነው በማለት ገልፀዋል።", "passage_id": "4a6425b19a8e364678ea2a7d9ddc035c" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሰራዊቱ በሰፈረባቸዉ ካምፖች የተከፈተበትን የከሃዲዎች ጥቃት በብቃት መክቶ ወደ ጸረ ማጥቃት እርምጃ መሸጋገሩን የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።ሰራዊቱ ተኩስ በተከፈተበት ካምፖች ሁሉ በጠንካራ መከላከል ውጊያ የከሃዲውን ሃይል በጀግንነት መክቶ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰበት ይገኛል፡፡የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊትና የአማራ የጸጥታ ሃይል ተቀናጅተዉ በሰሜን ጎንደር ዞን ቀራቅር በተባለ ቦታ የእብሪተኛዉ ቡድን የሰነዘረዉን የማጥቃት ውጊያ በብቃት በመመከት በዚህ ሃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ማቴሪያላዊ ኪሳራ አድርሶበታል፡፡ሰራዊቱ በዛሬዉ እለት ከሰዓት በኋላ በወሰደዉ ቅንጅታዊ የማጥቃት እርምጃ ከቀራቅር በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘዉ ከፍተኛ ቦታ ላይ የነበረዉን የእብሪተኛዉ አጥፊ ቡድን ሃይል በከፍተኛ ሁኔታ በማጥቃት ቦታዉን ቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል።ጀግናዉ ሰራዊት በወሰደዉ የማጥቃት እርምጃ በዚህ ነብሰ በላ ቡድን ሃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ ኪሳራ በማድረስ የቡድንና የነብስ ወከፍ መሳሪያዎችንም ማርኳል ፡፡", "passage_id": "b629bf8c2249b95681dc6dc2503cbce2" } ]
f521481ce72634358c44d9c83f5cbbba
9350d032ec1b27bf040345f12d9210c0
“መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ይፈለጋል”ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል የሰላም ሚኒስቴር
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግ ለሁሉም የሆነች አገርን በመገንባት ሂደት ላይ ሁሉንም ለማሳተፍ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ፡፡ትናንት በይፋ የተጀመረውን የብሔራዊ የማህረበሰብ ተኮር የምክክር መድረክን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተሰጠውን መሰረታዊ ተልዕኮ ለመወጣት ከባለድርሻዎች ጋር በትኩረት እየሰራ ይገኛል።እንደ አገር መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግም፤ ብዝሃነት ባለበት አገር ሁሉም ድምጾች እንዲደመጡ እድል መስጠት የሚያስችል ስራዎችን አቅዶ እየሰራ ይገኛል፡፡የሰላም ሚኒስቴር ከተሰጡት መሰረታዊ ተልዕኮዎች መካከል አንዱ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣ የህግ የበላይነት እና የዳበረ ዴሞክራሲ እንዲገነባ፣ እናም ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መስራት መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ ይሄን መሰረት በማድረግም በሁለት እርከን የተከፈለ ብሔራዊ የምክክር መድረክ ለማዘጋጀት ባለፈው አንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ሰፋፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ይሄም የመጀመሪያው መድረክ ሕብረተሰብ ተኮር የሆነ በየእርከኑ በተለይም ህብረተሰቡ የሚገኝበትን የመጨረሻውን እርከን ቀበሌን ማዕከል ያደረገ ምክክር የሚካሄድበት መርሃ ግብር ሲሆን፤ ሁለተኛው በተለያየ ደረጃ የሚገኙ ልሂቃን የሚሳተፉበት የምክክር መድረክ ነው።በዚህም ከትግራይ ክልል በስተቀር በሁሉም ክልሎች ህብረተሰብ ተኮር ብሄራዊ የምክክር መድረኩ በይፋ የተጀመረ ሲሆን፤ ለቀጣይ ሶስት ተከታታይ ወራት ያህል በቋሚነት የሚቀጥል ይሆናል፡፡ምክክር ልብ ለልብ መገናኘትን፣ መደማመጥን፣ መቻቻልን፣ እውን ለማድረግ፤ ችግሮችና አለመግባባቶች እንኳን ቢኖሩ ስልጡን በሆነ መንገድ በውይይት የመፍታት ባህልን የሚያለማምድ፤ ደረጃ በደረጃም ይሄንን መፍጠር የሚያስችል ልምምድ ነው።በኢትዮጵያ ላለፉት በርካታ ምዕተ ዓመታት ጥሩ ጥሩ እሴቶች ያሉንን ያህል ችግሮቻችንን በሰለጠነ መንገድ ተቀራርቦ ከመፍታት አኳያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተዳከመ የመጣ፤ በወጉም በተስተካከለ መሰረት ላይ ያልተገነባ እሴትና ባህል እንደመሆኑ መጠን፤ ችግርን በሃይማነ ጉልበት መፍታት አማራጭ ተደርጎ ሲወሰድ ቆይቷል።ይሄ ደግሞ የዴሞክራሲ ስርዓትን ለመገንባት ለሚተጋ አገር እጅግ አዳጋች የሆነ ጉዳይ ነው፡፡በመሆኑም በእነዚህ የውይይትና የምክክር መድረኮች ከአካባቢ ጉዳዮች ጀምሮ እስከ ብሔራዊናአገራዊ የሆኑ የጋራ የሆኑ ሀሳቦችና ጉዳዮችን የሚመለከት ስለሆነ የምክክር ሂደቱ መጨረሻ ላይ የሚያግባቡ አገራዊ ጉዳዮች ላይም የጋራ ድምዳሜ ይደረስበታል ተብሎ ይታመናል።ስለሆነም ትልቅ ዴሞክራሲን ለመገንባት ለምናደርገው ጥረት፤ ዘላቂ ሰላም ለመገንባት ለምናደርገው ጥረት መሰረታዊ የሆነ የእሳቤና የባህሪ ለውጥ ለማምጣት ያግዛል ተብሎ የተቀረጸ መርሃ ግብር ነው፡፡በዘሌ መንገድ ደግሞ ልሂቃን የሚያደርጉት ውይይት ተመሳሳይ ዓላማ ያለው ነው።ምክንያቱም ልሂቃን ሀሳብ የሚቀርጹ ናቸው።እናም የልሂቃን ሀሳብ በተስተካከለ መሰረት ላይ ማረፍ ከቻለ ለአገር ግንባታ ሂደት ትልቅ አበርክቶ ይኖረዋል።ስለዚህ ልሂቃንም በየፈርጃቸው አገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጓቸው ውይይቶች እና የሚደርሱባቸው መግባባቶች ተመልሶ በህብረተሰብ ደረጃ ለሚካሄደው ውይይት፤ በህብረተሰብ ደረጃ የሚካሄደው ውይይትም የሚያወጣቸው ሀሳቦችና የጋራ የሆኑ ጉዳዮች መልሶ የልሂቃኑን ሀሳብ መልክና ቅርጽ ለማስያዝ የራሱ አበርክቶ ይኖረዋል፡፡ይሄ የሁለቱ ምግግቦሽ በአንድ በኩል ከላይ ወደታች ህብረተሰቡ ላይ አጀንዳ የሚጫንበት ሳይሆን በራሱ ይመለከተኛል፣ ያሳስበኛል፣ የሚለውን ጉዳይ አንጥሮ የሚያወጣበት ይሆናል።በዚህም መንግስት ከእነዚህ መድረኮች የሚገኙ ግብዓቶችን ወስዶ ህብረተሰቡን ለማድመጥና ተግባራዊ ምላሽ ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።መጨረሻ ላይም የሁለቱ መድረከች በጋራ መጥተው ብሔራዊ የሆነ ምክክር፤ ስልጡን የሆነ ውይይት የሚደረግበት፤ የጋራ አቋም የሚወሰድበት ምዕራፍ ይኖረዋል፡፡እነዚህ ሁሉ ሂደቶች ለአገር ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል፤ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር ደግሞ ለአገር ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ያሉት ሚኒስትሯ፤ መድረኩ የልሂቃን ብቻ እንዲሆን ያልፈለግነውና መሰረተ ሰፊ እንዲሆን የፈለግነው መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ከዚህ አኳያ መሰረተ ሰፊ የሆነ ህብረተሰብ ተኮር ምክክር የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሌሎች ልሂቃን የሚሳተፉባቸው የምክክር መድረኮች ሲኖሩ፤ በጤናማ እና መሰረተ ሰፊ በሆነ ይዞታ ላይ የሚያርፍና የሚገነባ እንደሚሆን ተናግረዋል።ይህ ዘላቂ ለሆነ ሰላም ግንባታ የሚሆን የአገር ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም አስረድተዋል።የአገራት ልምድ የሚያሳየውም አገራት የአገር ግንባታ ሂደቶቻቸውን በየራሳቸው ነባራዊ ተጨባጭ ሁኔታ እንደየአመቺነቱ አስኪደውታል፤ በእኛ ተጨባጭ ሁኔታም ብዝሃነት ባለበት አገር ሁሉም ድምጾች እንዲደመጡ እድል መስጠት፤ ከዚህ ተነስቶም ለሁሉም የሚሆን አገር መስራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አብራርተዋል፡፡መድረኩም ይሄን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፤ በቀጣይ ወራትም ተጠናክሮ የሚቀጥልና በቋሚነት የሚሰራ መሆኑን፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱም ሁሉንም ባለድርሻ ለማሳተፍ የሚያስችል ስራ ማከናወኑን በመግለጽ፤ በቀጣይ ጥቂት ቀናት ከሚካሄዱ መድረኮች የሚገኝ ልምድም በዘላቂነት ለሚካሄደው መድረክ ተቀምሮ የሚሰራበት እንደሆነም አስረድተዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37844
[ { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 17፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገርን ሰላም በማስፈን የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት ግቡን እንዲመታ የሴቶች ሚና የጎላ መሆኑ ተገለፀ።በሀገር ሰላምና በዲምክራሲ ግንባታ ዉስጥ የሴቶች ተሳትፎ በሚል መሪ ቃል በጅግጅጋ ከተማ የሴቶች ኮንፍረንስ ተካሄዷል።በኮንፍረንሱ የሶማሌ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ኢንጂነር መሀመድ ሻሌ÷ ከዚህ በፊት በነበሩ የአስተዳደር ስርዓቶች ውስጥ ሴቶች የነበራቸው ተሳትፎ ውስን መሆኑን አንስተው ።አሁን ላይ የሁሉም መብት የተረጋገጠባት እና ሰላምና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ሀገር ለመገንባት ሴቶችን በሰፊው ማሳተፍ ተገቢ መሆኑን ገልፀው ከዚህ በኃላ በክልሉ የሚከናወኑ የአስተዳደር ስራዎች ሴቶችን በተገቢው መንገድ ያሳተፉ እንደሚሆን አረጋግጠዋል።የሶማሌ ክልል የመንግስት ኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አሊ በደል በበኩላቸው ሴቶች ለሰላምና ዲሞክራሲ ግንባታ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ዘርፎች ለሚመዘገብ ስኬት ሚናቸው የጎላ ነው ብለዋል።የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መንግስት አሁን ላይ ሴቶችን በተገቢው መልኩ ለማሳተፍ የጀመረው እንቅስቃሴ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለፅ በሀገሪቱ የሚፈለገውን ልማት ለማምጣትም ሴቶችን አሳታፊ ያደረገ የአስተዳደር ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ማንሳታቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።በተለይም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተከሰተው የፀጥታ መደፍረስ ሴቶችን ተጎጂ አድርጓል ያሉት ተሳታፊዎቹ ሰላምን ለማስፈን እና ዲሞክራሲን ለመገንባት ሴቶችን ማማከር ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል።", "passage_id": "10cc09900e68898bd7d94b76b5e4cc82" }, { "passage": "ጥቅምት 1 ቀን 2012 ዓ.ም ለመላ ኢትዮጵያውያን ታላቅ የድል ብስራት የተሰማበት እለት ነው። ምክንያቱም ደግሞ የዓለማችን ሃያላን አገራት መሪዎች ጭምር የሚመኙትና ለሰላም እውነተኛ ክብርና እውቅናን የሚሰጠው የሰላም የኖቤል ሽልማት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ በማቅናቱ ነው። የዚህ ሽልማት አሸናፊ ደግሞ ስለሰላም አብዝተው እየሰሩ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ናቸው። ዶክተር አብይ\nአህመድ ለዚህ\nክብር ከበቁባቸው\nበርካታ ጉዳዮች\nውስጥ አንዱ\nለ20 ዓመታት\nየዘለቀው የኢትዮ-ኤርትራ ሞት\nአልባ ጦርነት\nእንዲያበቃ በማድረግ\nሰላም ማስፈናቸው\nሲሆን ከዚህም\nባሻገር በአፍሪካ\nቀንድ ሰላምን\nለማምጣት ያደረጉት\nጥረትና ያስገኟቸው\nስኬቶችም ተጠቃሽ\nገድሎቻቸው ናቸው። በአገር ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች ለእስር ተዳርገው የቆዩ ዜጎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር እንዲፈቱ፣ የተለያዩ የፀረ ዴሞክራሲ ህጎች እንዲሻሻሉ እና የዴሞክራሲ ምህዳሩ እንዲሰፋ ያከናወኗቸው ተግባራትም ለሰላም ዘብነታቸው ማሳያዎች ናቸው።በአገር\nቤት ያለው የፖለቲካ ምህዳር ዝግ በመሆኑ ነፍጥ አንግበው ሲዋጉ የቆዩና በስደት ሆነው መንግሥትን በተለያየ አግባብ ሲታገሉ የነበሩ የፖለቲካ ሃይሎችም ወደአገራቸው ገብተው በሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ ያደረጉት ጥረት ተሳክቶ በርካታ ግለሰቦችና ድርጅቶች ወደ አገራቸው የተመለሱት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥረት እንደሆነ ይታወቃል። በሌላ በኩል\nለሴቶች የሰጡት\nክብርና እውቅናም\nየድላቸው ሌላኛው\nገጽታ ነው።\nበአገሪቱ የስልጣን\nታሪክ ውስጥ\n50 ከመቶ የካቢኔ\nአባላት ሴቶች\nየሆኑት በእኚሁ\nየሰላም ተምሳሌት\nመሪ ነው።\nእነዚህን ጉዳዮች\nመነሻ በማድረግ ነው ዓለምአቀፉ የኖቤል ሸላሚ ተቋም የዘንድሮውን የሰላም የኖቤል ሽልማት ያበረከተላቸው። ይህ ሽልማት ደግሞ ለአገሪቱ ጭምር ትልቅ ክብርና እውቅናን የሚያሰጥ ነው።ይህንን\nከግምት ውስጥ በማስገባትም በሰላም ሚኒስቴር አዘጋጅነት ትላንት በሚሊኒየም አዳራሽ “ሰላም መቶ በመቶ ያሸልማል” በሚል መሪ ሃሳብ ሀገራዊ የእውቅና አሰጣጥ ስነስርዓት ተካሂዷል። በዚህ የእውቅና ስነስርዓት ላይ የሰላም ሚኒስትሯ ክብርት ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል እንዳሉት፤ ይህች በዓለም ማህበረሰብ ዘንድ የኋላቀርነት፣ የርስ በርስ ግጭትና የረሃብ ምሳሌ ሆና የቆየች ሃገር በአዲስ ገጽ መፃፍ ጀምራለች ብለዋል። ወይዘሮ\nሙፈሪያት፣ አረንጓዴ ልማት፣ ማስታረቅ፣ የሴቶች እኩልነት፣ ሰላም የሃገራችን መገለጫዎች እየሆኑ መምጣታቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ፋና ወጊ መሆናቸውን ተናግረዋል።‹‹ሰላም ማለት የጦርነት እጦት\nብቻ አይደለም›› ያሉት ወይዘሮ ሙፈሪያት፤ የህዝቦች መከባበር፣ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴን በሰላም ማከናወን መቻል፣ ልጆች በሰላም ትምህርት ቤት ውለው የሚመለሱበትና እናቶች በሰላም ውለው የሚገቡበት፣ ትምህርት ቤቶች የሰላም ማዕከላት የሚሆኑበት፣ ፍትህ የሰፈነበትና በሰላም ወጥቶ መግባትን የሚመለከት መሆን አለበት ብለዋል። ሰላምን ማረጋገጥ ደግሞ የሰላም ሚኒስቴር ሥራ ብቻ ባለመሆኑ መላው ኢትዮጵያውያን ለሰላም የበኩላችንን አስተዋፅኦ ልናበረክት ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። ወይዘሮ ሙፈሪያት\nእንዳሉት፤ ሃገር\nመለወ ጫም\nሆነ መተኪያ\nየላትም፤ እኛ\nኢትዮጵያውያን ሃገራችን ላይ\nተረባርበን ከሰራን\nመስቀለኛውን መንገድ\nመሻገር እንችላለን።\nኢትዮጵያ መሪዎቿ\nወደሰነቁላት ማማ\nከፍ እንድትል\nከጥላቻና ከፅንፈኝነት\nርቀን በመተባበር\nልንሰራ ይገባል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ በበኩላቸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ስለሰላም ያበረከቱት አስተዋፅኦ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው ሥራ ነው ብለዋል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምን ለማምጣት ያደረጉት ጥረት ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው፤ በተለይ በሱዳን ያከናወኑት ተግባር ለአፍሪካ ሰላም አፍሪካዊ መፍትሄ እንዳለ ያሳየ መሆኑን በምሳሌነት አንስተዋል።የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት\nሳህለወርቅ ዘውዴ\nበበኩላቸው ባደረጉት\nንግግር አሁን\nበዓለም ላይ\nበርካታ የሰላም\nእጦት ችግሮች\nበሚታዩበት ነባራዊ\nሁኔታ ውስጥ\nጠቅላይ ሚኒስትር\nዶክተር አብይ\nአህመድ ይህንን\nሽልማት ማግኘታቸው\nለአገር ትልቅ\nክብር፣ ለህዝቦቿ\nታላቅ ደስታ\nነው። ‹‹እንዲህ\nአይነት ክብር በቀላሉ አይገኝም›› ያሉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ችግር ሲፈጠር ጎራ ይዞ ከመፋለም ይልቅ የመፍትሄ አካል መሆንን ይጠይቃል ብለዋል። ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት ሁሌም መፍትሄ አለ፤ የዶክተር አብይ ሽልማትም ዓለማቀፉ ማህበረሰብ የአገራችን ሰላም ላይ ተስፋ መጣሉን ያመላክታል ብለዋል። በቀጠናችን በርካታ\nሰላም ማስከበር\nሃይል ተሰማርቶ\nይገኛል ያሉት\nፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፤\nነገር ግን\nዘላቂ ሰላምን\nማስፈን አለመቻሉን\nጠቅሰዋል። በአንፃሩ\nግን ለዚህ\nሰላም ማስከበር\nሥራ የሚወጣው\nወጪ ለልማት\nቢውል የአካባቢውን\nችግር በከፍተኛ\nሁኔታ ሊፈታ\nበቻለ ነበር፤\nዛሬ በእጃችን\nየገባው የሰላም\nየኖቤል ሽልማት\nለሚቀጥለው ሰላምና\nየልማት ጉዞ\nእንደመስፈንጠሪያ ሊያገለግለን ይገባልም\nብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሁለት ሽልማቶች የተበረከተላቸው ሲሆን ከነዚህ ውስጥ አንዱ በአገራችን ትልቁና በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ ሽልማት ነው። ይህ ሽልማትም ከዚህ በኋላ በሰላም ዙሪያ ትልቅ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በየዓመቱ እንደሚሰጥ የሰላም ሚኒስትሯ ተናግረዋል። ሁለተኛው ሽልማት ደግሞ የሰላም ቤተሰቦች ሽልማት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድም ከሽልማቱ በኋላ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ክብርና ምስጋና ለኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ይድረስ ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመቀጠል በተለይ ለህፃናትና ታዳጊዎች ባስተላለፉት መልዕክት የእሳቸውን ልጅነት የህይወት ተሞክሮ አጋርተዋል። “እኔ በልጅነቴ እስከ ሰባተኛ ክፍል ድረስ መደብ ላይ ተኝቼ ነው የተማርኩት፣ ነገር ግን አሁን ያለው ትውልድ ከኔ የተሻለ፤ እድል አለው፤ በመሆኑም ከኔ የተሻለ፤ ቦታ እንደምትደርሱ እያሰባችሁ ተግታችሁ ልትሰሩ ይገባል ብለዋል። ሰላም ለኢትዮጵያ እና ሰላም ለአፍሪካ፣ እንዲሆን እያንዳንዳችን ሰላም ይኑረን፣ ለማሸነፍ መዋደድና ዝቅ ማለት ያስፈልጋል ሲሉም መክረዋል።ጠቅላይ\nሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከስኬታቸው በስተጀርባ ትልቅ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላትም ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ ከነዚህም መካከል በተለይ አቶ ለማ መገርሳ ላደረጉላቸው አስተዋፅኦ ሁሉ በማመስገን ከሰላም ቤተሰቦች የተበረከተላቸውን ሽልማት አብርክተውላቸዋል። በእለቱ “አብይ እንደ ሰው” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም የቀረበ ሲሆን፤ በፊልሙ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በእለት ተዕለት የህይወት እንቅስቃሴያቸውም ሆነ በኑሯቸው ውስጥ ለሰላምና ለፍቅር ያላቸው ከፍ ያለ ቦታ ተንጸባርቋል። ከዚህም ባሻገር በስራቸው ላይ ያላቸው ትጋትና ለሰው ልጆች ብልፅግና የሚያደርጓቸው ጥረቶች እንዲሁም ሩህሩህና አስተዋይ መሪ ስለመሆናቸው በአጭሩ ተዳሷል።አዲስ ዘመን ጥቅምት 10/2012ወንድወሰን ሽመልስ", "passage_id": "d593cd6537cbdae9d15744185c42fae0" }, { "passage": "የሰላም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ዓርብ ጥቅምት 30 ቀን 2011 ዓ.ም.፣ ወሎ ሠፈር አይቤክስ ሆቴል አካባቢ በሚገኘው ጽሕፈት ቤታቸው ከጋዜጠኞች ጋር ትውውቅ አድርገዋል፡፡ በዚህም ወቅት በቅርቡ የተቋቋመው የሰላም ሚኒስቴር ለመሥራት ስላቀዳቸው ተግባራት አጠር ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በዚህ መሠረት የሰላም ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑ መሥሪያ ቤቶችን መገምገሙን፣ ዘርፉ ለመጪዎቹ አሥር ዓመታት የሚመራበትን ፍኖተ ካርታ ጨምሮ በርካታ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን ለመመለስ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ከኅዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ለአንድ ዓመት የሚቆይ መላውን ኅብረተሰብ ያካተቱ የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚኖሩ፣ በዚህም መሠረት የሰላም አቀንቃኝና መልዕክተኛ እንደሚመረጥ፣ በመርሐ ግብሩ መጨረሻ ደግሞ አገር አቀፍ የሆነ የሰላም ሽልማት እንደሚኖር ገልጸው፣ በዚህም መርሐ ግብር ለሰላም የዘመሩና የኖሩ ዕውቅና ይሰጣቸዋል ብለዋል፡፡ በምሥሉ ላይ ሚኒስትሯ ከጋዜጠኞች ጋር የእጅ ሰላምታ ሲለዋወጡ ይታያሉ፡፡ ", "passage_id": "176d5939a64953b2e7c852d7be3a571e" }, { "passage": "ባሕርዳር፡ ጥቅምት 13/2013 ዓ.ም (አብመድ) በከተሞች ለሰላም እጦት መንስኤ የሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አስታወቁ፡፡\nፕሬዝዳንቷ ይህን ያስታዎቁት በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ባለው የከተሞች የሰላም ፎረም ላይ ነው፡፡ “የፍትህና ተጠያቂነት መጓደልና ስራ አጥነት በከተሞች የሚስተዋሉ ዋና ዋና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ናቸው” ብለዋል፡፡ችግሮቹን ለመፍታት ከህዝቡ ጋር በግልጽ ውይይት መደረግ እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡ የከተሞች ሠላም ለሀገራችን ዘላቂ ልማት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ በፖሊሲ ሊደገፍ እንደሚገባ አስታውቀዋል።ኢዜአ እንደዘገበው የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ያዘጋጀውና “ከተሞችና ሰላም” በሚል መሪ ቃል በአርባምንጭ እየተካሄደ ባለው የከተሞች ፎረም ላይ ሚኒስትሮች፣ የክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽ ቢሮ ኃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።", "passage_id": "b0428972a6dc087f1a6837beed9298c2" }, { "passage": ")-5ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የሀገሪቱ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ ዴሞክራሲ አንድ እርምጃ ወደፊት እንዲራመድ ያደረገ ተግባር ማከናወኑን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሚኒስትር ሬድዋን ሁሴን አስታወቁ።የሀገሪቱ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዘርፍ በ5ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የነበረውን ሚናና በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን በሚያተኩርባቸው ተግባራት ላይ ከፍተኛ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን አመራሮች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተካሄዷል።የመንግስት ኮሙዩኒኬን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፥ የሀገሪቱ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ በ5ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ሒደት ሁለት ዓበይት ሚናዎች ነበሩት።የዘርፉ ቀዳሚ ሚና በህዝቡ ውስጥ የሚነሱ ጥያቄዎችና ችግሮች አሰባስበው በማስተጋባት መፍትሔ እንዲያገኙ ማድረግ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሰላምን ፋይዳ በመገንዘብ ሠላምን የሚያደፈርሱ አደጋዎችን ለይቶ በማሳወቅ ህብረተሰቡ እንዲከላከላቸው ማድረግ እንደነበር ሚኒስትሩ ተናግረዋል።በምርጫው ሒደት የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ የፈፀማቸው ተግባራት ዴሞክራሲያችን አንድ እርምጃ ወደፊት እንዲራመድ ገንቢ ሚና ቢጫወትም ዘርፉ አዳጊ በመሆኑ ጥቃቅን ስህተቶችና ክፍተቶች ነበሩት ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡መልካም ተሞክሮዎችን በመቀመርና ክፍተቶቹን በመሙላት በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን የበለጠ ተግቶ እንዲሰራ የምክክር መድረኩ ጠቀሜታ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።ከምርጫው በፊት ምርጫው በሠላማዊ መንገድ እንዳይካሔድ የሞከሩ ሃይሎች እንደነበሩ ያስታወሱት ሚኒስትር ሬድዋን፥ ለሁከትና ብጥብጥ ያዘጋጁዋቸው ስልቶች ህዝቡ ቀድሞ እንዲያውቃቸውና እንዲከላከላቸው በማድረግ ዘርፉ ገንቢ ሚና መጫወቱን አስረድተዋል።የሀገር ውስጥ የግል ሚዲያዎችን በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል ያሉት ሚኒስትሩ በአንድ በኩል የራሳቸው የሆነ ቋሚ በጀት መድበው የማይንቀሳቀሱ ግን ደግሞ የውጭ አካላት የሚያራግቡትን ተቀብለው የሚያስተጋቡና ሁከት፣ ረብሻና የመንግስት ግልበጣ የሚሰብኩ ናቸው ብለዋል።አንዳንዱ ደግሞ ሀገራቸው ነውና የአቅማቸውን ያክል ጉድለትን አጋንነው የሚናገሩ በጎ ነገር ደግሞ በልኩ ለመናገር የሚሞክሩ ናቸው ያሉት አቶ ሬድዋን አብዛኛዎቹ በጎ አስተዋፅኦ እንደነበራቸው ገልፀዋል።የውጭ ሚዲያዎች የውጭ ናቸውና የውጭ አመለካከት ይዘው አንዳንዱ ኢትዮጵያ ላይ የሃሰት ውንጀላ የሚያቀርቡ የሊቨራል አቋም አራማጆች ናቸው’ ያሉት አቶ ሬድዋን፥ ምንም በጎ ነገር ቢሰራ በጎ አይደለም ብለው የሚከራከሩ በጎ መሆኑን በተግባር ስታሳያቸው ደግሞ ከበጎ ድርጊቱ በስተጀርባ ሌላ ነገር ሊኖር ይችላል ብለው የሚሞግቱ ናቸው ብለዋል።መንግስት በምርጫው ሒደት በርካታ ዓለም አቀፋዊ ሚዲያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ፈቃድ በመስጠት፣ የፌዴራልና የክልል ተቋማት የፈለጉትን መረጃ እንዲሰጡዋቸው በማመቻቸትና በየትኛውም ቦታ የፈለጉትን ሰው በማነጋገር እውነታውን እንዲገነዘቡት በማድረግ በአገር ገፅታ ግንባታ ላይ በጎ አስተዋፅኦ እንዲጫወቱ ለማድረግ ተሞክሯል ብለዋል።የውጪ ሚዲያዎች በቆይታቸው በኢትዮጵያ ውስጥ በገመቱትና በተግባር ባዩት መካከል ሰፊ ልዩነት መታየቱን፣ ጥፋት ሳይሆን በተጨባጭ ልማት መኖሩን፣ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ለምን ገዥው ፓርቲ እንደመረጠና ሌሎች እውነታዎችን ተገንዝበው እንዲመለሱ መደረጉን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።በምክክር መድረኩ ላይ የተሳተፉ የፌዴራልና የክልል የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ከፍተኛ አመራሮች የምርጫውን ሒደት ሠላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነፃ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ባከናወኑት ስራ ያዩዋቸውን መልካም ተሞክሮዎችና ክፍተቶች በማስረጃ እያጣቀሱ አቅርበዋል።(ኤፍ.ቢ.ሲ)", "passage_id": "b290b103c4ace9f3bcf3d7f5b3d03acf" } ]
af019b8137733d4223220dc58ff5c360
aab9363fc20cec83af702f8728038a5c
“በኃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ይጎዳል እንጂ አይጠቀምም ” ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ጥሩ አላማ እና ህዝብ ይጠቅማል የሚል ሃሳብ ይዞ ከመቅረብ ያለፈ በሃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ማንኛውም ኃይል ከመጎዳት ያለፈ ምንም እንደማይጠቀም የህወሓት ጁንታ አፍኗቸው ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ ተናገሩ።መከላከያ ሰራዊቱም በሰላማዊ መንገድና በዴሞክራሲያዊ አካሄድ የሚመጣውን ብቻ ተቀብሎ ለመሄድ የሚሰራ እንደሆነም አስገንዝበዋል።ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ እንደተናገሩት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ለዓመታት የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ላይ ተጠምዶ ከማሳለፉ ባሻገር በሃይል ወንበር ለመያዝ እንዲያመቸው በመከላከያ ሰራዊቱ አባላት ላይ የፈጸመው ጥቃት ውድቀቱን አፋጥኖለታል።መከላከያ ሰራዊቱም ለዚህ የሚመች ሃይል አለመሆኑን አሳይቷል።በመሆኑም የተሻለ ዓላማ ለህዝብ በሚጠቅም ሃሳብ ይዞ ከመስራት ባለፈ በሃይል ወንበር ለመያዝ የሚደረግ ሙከራ የማይጠቅም፤ ይልቁኑም ያንን ኃይል የሚጎዳ መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡እንደ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ ገለጻ፤ የጁንታው ቡድን በህዝቡ ውስጥ ብቻ ሳይሆን መከላከያ ሰራዊትን የማጠልሸት እና የመከፋፈል ስራዎች ቀድሞ ሲያከናውን ነበር። ሰራዊቱ በአንድ መምሪያ እና ተቋም ስር ሆኖ ሳለ የሰሜን እዝ መጥፎ ነው ምዕራብ አሊያም ምስራቅ ዕዝ ጥሩ ነው የሚል መከፋፈል ሲታይ ቆይቷል። በማህበራዊ ድረገጾች እና በአካል ጭምር ሰራዊቱን የማጠልሸት ስራዎችን አከናውነዋል፤ በቻሉት መጠን የሰራዊቱን የውስጥ አንድነት ያናጋል ብለው የሚያስቡትን ለማድረግ ያልወረወሩት ጠጠር የለም። ሆኖም ችግሮቹ ከዛሬ ዛሬ ይስተካከላሉ በሚል ሀገር ተመልሳ ወደጦርነት እንዳትገባ ነበር ሰራዊቱ ነገሮችን በትዕግስት ለማለፍ የመረጠው። በዚህ መሃል ግን ሰራዊቱ ህይወቱን ብቻ ሳይሆን ከኪሱ አዋጥቶ ለህዝብ እያገዘ ባለበት ሥፍራ የጁንታው ቡድን የአፈና ተግባር የማፍያ ቡድንነቱን ያሳየበት ስራ ነው። ይሄን ተከትሎም በመንግስት በኩል የተሰጠው አቅጣጫ እና በመከላከያ ሰራዊቱ የተወሰደው የማጥቃት እርምጃ ደግሞ አገርን ከጥፋት የታደገ፤ በሃይል ስልጣንና ወንበር ለመያዝ ማሰብ ትርፉ ለራስ መጥፋት ምክንያት መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ክስተት ሆኖም አልፏል፡፡በዚህ ረገድ ህግን በማስከበር እርምጃው በመንግስትም ሆነ በመከላከያ ሰራዊቱ በጥበብና ጥንቃቄ በተመላበት መልኩ የተወሰደው ለመንግስትምለሰራዊቱም አድናቆትና ምስጋና የሚያስቸረው ነው።በቀጣይም የጁንታው አመራር አባላት ከያሉበት ተይዘው ለፍርድ እንዲቀርቡ ያደረግ ሲሆን፤ እኛም የጁንታው ቀሪ ቡድን ተይዞ ለህግ እንዲቀርብ የሚደረገው ጥረት ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ ነን፣ ሲሉ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ ተናግረዋል።መከላከያ ሰራዊት ከፖለቲካ ነጻ ሆኖ እንዲሰራ የተጀመረው ስራ እንዲጠናከር እንሰራለን ያሉት ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም በምርጫ ከተሸነፉ ስልጣን ለመልቀቅ ፍቃደኛ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ከማሳወቃቸው ጋር ተያይዞም መከላከያ ሰራዊቱ በሰላማዊ መንገድና በዴሞክራሲያዊ አካሄድ የሚመጣውን ተቀብሎ ለመሄድ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡በመሆኑም ጥሩ አላማ እና ህዝብ ይጠቅማል የሚል ሃሳብ ይዞ ከመቅረብ ያለፈ፣ በጉልበትና በሃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ኃይል ቢኖር የሚጎዳ እንጂ የሚጠቀም አለመሆኑን መገንዘብ እንዳለበት አሳስበዋል።ችግር ቢኖር እንኳን በሃይል ሳይሆን በቀጣይ ችግሮችን አርሞ እና አሻሽሎ መምጣት አስፈላጊ መሆኑን በመጠቆምም፤ ለተወሰነ የስልጣን ፈላጊ ቡድን ሲባል ብሔር ብሔረሰቦች በማንነታቸው፣ ባህላቸውና በወጋቸው ላይ ድርድር ስለማይኖር ሁሉም አካል ህዝብን መሰረት አድርጎ መስራት እንደሚገባው ተናግረዋል፡፡እንደ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ ገለጻ፤ የአንዱ መብት መከበር የሌላኛው መከበር፣ የአንዱ መብትና ጥቅም አለመከበርም የሌላኛው አለመከበር መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።ከዚህ ባለፈ ደግሞ የጋራ እሴቶች ላይ መሰራት ይኖርበታል። ጁንታው ግን በጋራ አንድነት ላይ የማዳከም እና ሁሉ ነገር ላይ መሰማት አለብኝ ሲል እና ሌሎች የተናገሩት ውሸት እኔ የተናገርኩት ግን እውነት ነው ብሎ ሲያምታታ የኖረ እንደመሆኑ በፍላጎቱ ተመርቶ ሞቱን አፋጥኗል።በመሆኑም ከዚህ ትምህርት ወስዶ ሁሉም አካል የጋራ ተጠቃሚነት የሚያበለጽጉ አካሄዶችን በማዳበር ድህነትን ለማስወገድ መስራት፤ ወንበርም ከጦርነት ይልቅ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመያዝ ልምድን ማዳበር ይኖርባቸዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37845
[ { "passage": "ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 27/2013 ዓ.ም (አብመድ) ወቅታዊውን የሃገሪቱን የፀጥታ ሁኔታ አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል እንደሻው ጣሰው ህወሃት ህዝብ እና ሃገርን ለጥበቃ በተሰማራ የመከላከያ ሰራዊት ኃይል ላይ ጥቃት መፈፀም ክህደት ነው ብለዋል፡፡ “ጥቃቱን ታሪክ፣ ህግ እና ህሊና ይቅር የማይለው ነው›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡በትግራይ ክልል በሚገኙ 22 ትልልቅ የህዝብ እና የመንግስት ተቋማት ላይ የፌደራል ፖሊስ ተልዕኮ ተሰጥቶት ጥበቃ ያካሂድ ነበር ያሉት ኮሚሽነሩ ህወሃት በርካታ ኃይል በመመደብ በአባሎቻችን ላይ ጉዳት አድርሷል ብለዋል፡፡ በአካባቢው የሚገኘው የፌደራል ፖሊስ አሁን ላይ ከጥቃት ወጥቶ በቅንጅት ወደማጥቃት ተመልሷልም ብለዋል በመግለጫቸው፡፡የትግራይ ህዝብ የእለት ከእለት እንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎል እና የመንግስት አገልግሎት እንዳይቋረጥ የፌደራል ፖሊስ ህግ የማስከበር ስራውን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡ በትግራይ ክልል ትልልቅ የመንግስት እና የህዝብ ተቋማት ላይ የፌደራል ፖሊስ ተልዕኮ ተሰጥቶት ጥበቃ እያካሄደ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡በተለያዩ አካባቢዎች ህግ የማስከበር ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን የገለፁት ኮሚሽነር ጀኔራል እንደሻው አሁን ደግሞ በሃገሪቱ ትልልቅ ከተሞች ጥፋት እንዲፈፀም ኃይል መሰማራቱ ተደርሶበታል ነው ያሉት፡፡ ጥቃት እንደሚፈፀም ከህዝብ ከደረሰ 1 ሺህ 500 በላይ ጥቆማ ውስጥ በርካቶቹ ትክክለኛ መሆናቸው ተረጋግጧል፤ በርካቶቹን በህግ ቁጥጥር ስር አውሎ የምርመራ ስራ መጀመሩን እና በቀሪዎቹ ላይ ደግሞ የክትትል ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡ህዝቡም መንግስት የሚሰጠውን መልዕክት እየተከታተለ ተልዕኮውን እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ዘጋቢ፡- ጋሻው ፋንታሁን – ከአዲስ አበባ", "passage_id": "e981e833c44fc3a9e5732b8cbffa070c" }, { "passage": "“አይረጋጉም፣ አደገኛ ናቸው፤ አስፈሪ ናቸው፤ የተባሉ የጦር ቀጣናዎችን በብቃት አረጋግቷቸዋል”ባሕር ዳር፡ ኅዳር 08/2013 ዓ.ም (አብመድ) በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በወቅቱ ምደባ በእጣ ነበርና የቀጣይ የመምህርነት ሕይዎታቸው መከላከያ ሚኒስቴር ሆነ፡፡ ሠራዊቱ ባለበት የሀገሪቱ አካባቢዎች ሁሉ እየተዟዟሩ የቀለም ትምህርት አስተምረዋል፡፡ሠራዊቱ ያረፈባቸው፣ ያካለላቸውና የተጓዘባቸው አካባቢዎች ሁሉ አብረው አሉ፤ ለ17 ዓመታትም አገልግለዋል፣ አቶ አብረሃም ግርማይ፡፡ ምንም እንኳን አሁን ላይ የሥራ ዘርፍ ቀይረው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ እየሰሩ ቢሆንም በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ስለነበራቸው ጥዑም የሥራ ዘመን አውርተው አይጠግቡም፡፡ሥለ ሰሞኑ በትህነግ ከሀዲ ቡድን በሰሜን እዝ ላይ ስለፈጸመው ክህደት እና ስለ ኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጀብድ በተመለከተ በስልክ ሲናገሩ የእንባ ሳግ ሲተናነቃቸው ከድምጻቸው በግልጽ ይታወቅ ነበር፡፡የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን የክህሎት፣ የእውቀት እና የአመለካከት ብቃት ጠንቅቀው ያውቁታል፡፡ አቶ አብረሃም “ወታደር ባልሆንም እንደ አንድ ብዙ ዓመታትን አብሮ እንደሠራ ሰው መከላከያ ሰራዊታችን በደንብ ነው የማውቀው” ብለዋል፡፡የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የጀግንነት ታሪኩ ከኢትዮጵያ ሕዝብ የወጣ መሆኑ፣ ለሀገር ያለውን ጥልቅ ፍቅር፣ በተሰማራባቸው የጦር አውዶች የፈጸማቸውን ጀብዶች፣ አዲስ ነገር ለማወቅ ያለውን ጥልቅ ፍላጎትና ሌሎች ጥንካሬዎቹንም ጠቅሰዋል፡፡እንደ አቶ አብረሃም ግርማይ ማብራሪያ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በተቀረው ዓለም ጭምር መልካም የሚባል ሥም አለው፡፡በሠላም አስከባሪነት በተሰማራባቸው የውጭ ሀገራት ጭምር በጀግንነት፣ በወታደራዊ ጥብቅ ዲሲፕሊን እና በሰብአዊነት ግዳጁን በሚፈለገው ልክ ስለሚወጣ በሕዝቡ ክብር የሚሰጠው መሆኑን አብረው በተጓዙባቸው ጊዜአት ማረጋገጣቸውን ገልጸዋል፡፡“አይረጋጉም፤ አደገኛ ናቸው፤ አስፈሪ ናቸው፤ የተባሉ የጦር ቀጣናዎችን ጭምር የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በብቃት አረጋግቷቸዋል፤ የላይቤሪያ የእርስ በርስ ጦርነት የኢትዮጵ መከላከያ ሠራዊት ሲገባ ነው የተረጋጋው፤ ከዚያ በፊት ሌሎቹ ሞክረው አልተሳካላቸውም፤ ጀግና እና ዓለም የሚያደንቀው ሠራዊት ነው” ሲሉ እርሳቸው አብረው የተሳተፉበትን እና የተመለከቱትን ለአብነት አንስተዋል፡፡በቡሩንዲ፣ ሩዋንዳ፣ ሱዳን ዳርፉር፣ አብዬ፣ ላይቤሪያና ሶማሊያ ያስመዘገባቸውን ደማቅ ዓለም አቀፋዊ ጀብዶች ጠቅሰዋል። አልሸባብን እና መሰል የሀገርን ብሎም የቀጣናውን ጠላት መደምሰስ፣ ዜጎችን ከጥቃት መከላከል፣ የአካባቢው ሠላም እንዲረጋገጥ የተሰጡትን ኃላፊነቶች በብቃት መወጣቱን አስረድተዋል፡፡የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ስንቁን እያካፈለ ብዙዎችን መግቧል፤ ለሕይዎቱ ሳይሳሳ፣ ለጉልበቱ ሳይሰስት ኅብረተሰቡን አገልግሏል፤ ከደሞዙ በመቀነስ ትምህርት ቤት እና መሰል የሕዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ገንብቷል፤ ይሄን አቶ አብረሃም ሠራዊቱ በ1996 ዓ.ም በላይቤሪያ ሠላም ለማስከበር በተባበሩት መንግስታት ጥላ ስር በተሰማራበት ግዳጅ ወቅት አብረው ተጉዘው ተመልክተዋል፡፡የኢትዮጵያዊነት ፍቅር በሕዝቡ ልብ ውስጥ እንዲሰርጽ በመስራቱ ከሌሎቹ ሀገራት ሠላም አስከባሪ ሠራዊት በተለየ ሁኔታ በላይቤሪያ ሕዝብ ዘንድ ክብር እና ተቀባይነት እንደነረበውም ህያው ምስክር ሆነዋል፡፡“እኔ ሠራዊቱን የምገልጽበት ቃላት ያጥረኛል፤ ሰው አክባሪ፣ ለአንተ ምቾትና ክብር እጅግ አብዝቶ የሚጨነቅ፣ ከሁሉም ነገር አስቀድሞ ለአንተ የሚሳሳ ሠራዊት ነው” ሲሉ ገልጸውታል አቶ አብረሃም፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሀገሩ የሰጠቸውን አደራ በብቃት የሚወጣ፣ ብቃት ያለው፣ ክብር ሚገባው ሠራዊት እንደንደሆነም አስረድተዋል፡፡በትህነግ ከሀዲ ቡድን የተፈጸመው ክህደት አሳፋሪ እና አሳዛኝ እንደሆነና በራሱ ጓዶች ተከድቶ እንደገና ራሱን አደራጅቶ ከሀዲውን ቡድን ወደ መደምሰስ መሸጋገሩ ምን ያህል የላቀ ብቃት ያለው ሠራዊት መሆኑን እንደሚያሳይ ነው አቶ አብረሃም ተናግረዋል፡፡በተፈጸመበት ክህደት በቁጭት እና በጀግንነት የትህነግን ጁንታ ቡድን እየደመሰሰ ወርቃማ ድሎችን እያስመዘገበ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ “ሠራዊቱ ወደ እንደዚህ አይነት ድል መሸጋገሩ ብቃቱ የቱን ያህል የላቀ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፤ እጅግ በጣም እንድትኮራበት የሚያደርግህ ሠራዊት ነው፤” ብለዋል።", "passage_id": "a6f4b7bb22bd82567ce1bff0dfb5cdd9" }, { "passage": "በአስመረት ብስራት\n\nበትምክህት የደነደነ ልብ ሳይሆን በጦረነት እውቀትና በስልጠና የፈረጠመ ጡንቻ ያለው ኢትዮጵያዊነት የገባው ወታደር ሁልጊዜም የድል ባለቤት መሆኑን ብርጋዴር ጀኔራል ካሳዬ ጨመዳ አስታወቁ።ብርጋዴር ጀኔራሉ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እንደተናገሩት፣ የህውሓት ጁንታ ቀደም ሲል ከ15 ዓመታት በላይ ሲዋጉ ጠንካራ የሚገዳደራቸው ወታደር ነበር፤ አሁንም ለሀገሩ የሚዋጋ ጠንካራ አቅም ያለው የመከላከያ ሠራዊታችን የቀደመ ታሪካቸውን እንዲያስታውሱ አድርጓቸዋል።ድሮም ምንም አቅም ምንም እውቀት ኖራቸው አያውቅም ነበር ያሉት ብርጋዴር ጀኔራል ከሳዬ፣ ባዶ ውሸትና ትምክህት ብቻ በሞላው ልባቸው ወደጦርነት በመግባታቸው የሽንፈትን ፅዋ ለመጨለጥ ተገደዋል ብለዋል። ድሮም ወደ ስልጣን መምጣት የቻሉት የተዋጊነት አቅም ኖሯቸው ሳይሆን በደርግ መንግሥት ስህተትና ድክመት ህዝቡ መሰላቸት እና የሀያላን ሀገር ጣልቃ ገብነት በመጨመሩ እንደነበር ጠቁመዋል። በህውሓት ጁንታ አሁን በጠላትነት የተፈረጀው የኢትዮጵያ ህዝብ እያበላ፥ እያጠጣ፥ መንገድ እየመራ ደጀን መሆን ደግፎ ወደስልጣን አወጣው እንጂ በፊትም ወታደራዊ ብቃት እንዳልነበራቸው አስታውቀዋል። ለዚህ ውለታው ህዝቡን በዘር በመከፋፈል ከማጫረስ በስተቀር ምንም ሳይጠቅሙት መኖራቸውን ገልጸዋል።የህዝብ ዕንባ የመከላከያ ሠራዊቱ ጥንካሬ ከዚህ ቡድን ነፃ ስላወጣን ምስጋና ሊቸረው ይገባል ብለዋል።በባዶ ጉራ ሙሉ የመከላከያ ሠራዊቱን በቁጥጥራቸው ስር አውለው፤ በጦር መሳሪያና በሹመት ብዛት የሚያሸንፉ መስሏቸው ሲፎክሩ ቆዩ እንጅ ወታደራዊ ብቃት ያለነበራቸው ቡድኖች መሆናቸውን መከላከያ ሠራዊታችን በገልፅ አሳይቷል ያሉት ብርጋዴር ጀኔራል ካሳዬ፣ ለሁሉም ደባና ተንኮል የሚያስከፈለውን ዋጋ በአግባቡ ለመመልከት እንደቻሉ ጠቁመዋል።የተዋጊያቸውን አቅም ያላገናዘቡት እነዚህ ተንኳሽ ቡድኖች ዘመኑ የቴክኖሎጂ መሆኑን ሳያስተውሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈው ጦር ሠራዊታችን ባሳየው የኃይልና የእውቀት ብልጫ ትምክህተኛውን ለማሸነፍ መቻሉ የሚያኮራ ይበል የሚባል ተግባር መሆኑን አመልክተዋል።የትግራይ ህዝብ ኢትዮጵያዊነቱን የሚያከብር ህዝብ መሆኑን እዚህ በተገኘሁበት ወቅት ተመልክቻለሁ የሚሉት ብርጋዴር ጀኔራል ካሳዬ፣ እንግዳ የሚቀበል ሰው አክባሪ የሆነ ጠንከራ ህዝብ መሆኑን ገልጸዋል። ሀገርን እኛ ካላስተዳደርን ይፍረስ ብሎ መዝለል ተገቢ እንዳልሆነም ጠቁመዋል። ከአንድ መቶ ሚሊዮን ህዝብ በላይ ያለባት ሀገር ሁሉም ህዝብ ወንበር መያዝ ቢፈልግ የማይችል መሆኑን አስረድቶ ሁሉም በያለበት ሀገርን የማሳደግ ኃላፊነትን ከመወጣት ባለፈ የግድ ልምራ ማለት ፍትሐዊ ያልሆነ ጥያቄ እንደሆነ ገልጸዋል።የትግራይ ህዝብ ከዚህ በፊትም ታፍኖ የኖረ አሁንም ታፍኖ ነው ያለው ህዝቡ ፤ ህዝቡ በስሙ ተነገደበት እንጂ ምንም ያልተሠራለት ዛሬም ይህ ህዝብ የተራበ የተጠማ እንደሆነ አመልክተዋል። ልጆቹ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው የሚማሩ ናቸው። የህውሓት ጁንታ ለፕሮፖጋንዳ የሚያሳዩትን ያህል ሳይሆን በጥልቀት ሲታይ በችግር እንዲኖር ያደረጉት ይህን የተጎዳ ህዝብ በመካስ ይህን ጨዋ ህዝብ ወደ እውነተኛ ማንነቱ መመለስ ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ይጠበቃል ብለዋል።\n\n", "passage_id": "ba95852ad5e5b35cca801c316cbb1fad" }, { "passage": "በኢትዮ-ኤርትራ መካከል ሰላም በመስፈኑና ስጋት በመወገዱ ፣ በመከላከያ በተካሄደው ሪፎርም ስድስት የነበሩት ዕዞች ወደ አራት ዝቅ በማለታቸው በሰሜን ድንበር አካባቢ የነበረውን የተወሰነው የመከላከያ ሰራዊት ወደ ሌሎች የኢትየጵያ ክፍሎች የማንቀሳቀስ ስራ እየተሰራ  መሆኑን በቅርቡ የኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡የልዩ ዘመቻዎች ሀይል አዛዥ ሌተናል ጀነራል ሞላ ሀይለማርያም፣ በኤርትራ በኩል ያለው ስጋት በመወገዱ ምክንያት በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ከነበረው ሰራዊት የተወሰነው ወደ ሌሎቹ የአገሪቱ ክፍሎች የሚንቀሳቀሰው ህዝቡ ያለ ስጋት መኖር እንዲችልና የሜጋ ፕሮጀክቶችን ደህንነት ለማረጋገጥ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል  በብዛት ተሰባስቦ የሚገኘውን የመከላከያ ሀይል ወደ ሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች የማንቀሳቀስ ስራዎች የሚሰሩባቸው ምክንያቶችም የኢትዮ-ኤርትራ የሰላም ሁኔታ በአብዛኛው የተሻለ ሁኔታ በመድረሱ፣የሁለቱ ህዝቦችና መንግስታት የሰላም ፍላጎታቸው የተረጋገጠ በመሆኑ፤ የክልሎችን የጸጥታ ሀይሎች አቅም ለማጠናከር፣ የሁሉንም የአገሪቱ ክፍሎች ደህንነት ለማስጠበቅ መሆኑንም ይገልጻሉ፡፡ይህ ማለት ግን ከባድሜና ሌሎች አካባቢ ሰራዊቱ ሙሉ ለሙሉ ይወጣል ማለት እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል፣በሁሉም የአገራችን አካባቢዎች ሊገጥም የሚችለውን የጸጥታ አደጋ መከላከል በሚያስችል መልኩ አሰፋፈሩ ተወስኖ ወደ ስራ መገባቱን ሌተናል ጀነራል ሞላ ጠቅሰዋል፡፡መንግስት ሰራዊቱን ሲያንቀሳቅስ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ገምግሞና ሌላ ዓላማ የለውም የሚል እምነት ስላለኝ እንደ ትልቅ ስጋት አላየውም የሚሉት የቀድሞው አየር ሀይል አዛዥ ሜጀር ጄነራል አበበ ተክለሀይማኖት፣ ነገር ግን ስጋት አላቸው፡፡‹‹ፕሬዚዳንት ኢሳያስ  ነገ ምን ሊያደርግ እንደሚችል ባህሪውን አውቀዋለሁ ፡፡ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ መናገር የሌለበት ቢሆንም አሁንም በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይ እንደፈለገ ነው እየተናገረ ያለው›› የሚሉት ሜጀር ጄነራል አበበ፤ ከኤርትራ ጋር ሙሉ ለሙሉ ሰላም መጥቷልና ሰራዊት ላንቀሳቅስ ማለቱ ተገቢ አይደለም ሲሉ ሞግተዋል፡፡‹‹ሌሎቹ እንደሚሉት የእኛን ጠቅላይ ሚኒስትር የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ እየመራው ነው የሚል እምነት ባይኖረኝም፡፡ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ ግን እንደፈለገ እንዲናገር መፈቀድ የለበትም የሚል እምነት አለኝ፡፡ እርግጥ ነው ሙሉ ለሙሉ ሰላም ከተፈጠረ ድንበሩ በሚሊሻም ሊጠበቅ ይችላል፡፡ አሁን ግን ሙሉ ለሙሉ ተማምኖ ሰራዊትን ማንቀሳቀስ ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡ ምክንያቱም ፕሬዚዳንቱ ከህወሓት ጋር ባላቸው ቁርሾ ምክንያት  ስጋት ሊፈጥር ይችላል፡፡ ስለዚህ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡‹‹ሌሎቹ  ወገኖች ሰራዊቱ መንቀሳቀስ የለበትም የሚሉትና ስጋት የፈጠረባቸው  ከጥርጣሬና ከፌዴራል መንግስቱ ጋር ካላቸው የሻከረ ግንኙነት ጋር አስተሳስረው ነው ፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ ባድመ ሲወረር ሚሊሻ ብቻ ነው በአካባቢው የነበረው፡፡ እዚህ ላይ ጥንቃቄ አድርጎ የተከማቸ ሰራዊት ካለ ወደ ሌላው ማንቀሳቀስ ችግር የለውም›› ሲሉ ሃሳባቸውን ቋጭተዋል፡፡‹‹በአሁኑ ወቅት መንግስት ዋና ስጋቴ ነው የሚለው ከውጭው ይልቅ አገር ውስጥ እየሆነ ያለው ነገር ነው፡፡ ምክንያቱም የውጭው ስጋት የአገሪቱ ውስጣዊ ሁኔታ ላይ ተመስርቶ  የሚመጣ ነው›› የሚሉት ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ፣በተለያዩ ግለሰቦች አቀናባሪነትና ፈጣሪነት የጎሳ ግጭት የሚመስል ግን ደግሞ መደበኛ የሰራዊት ውጊያ አይነት ክስተት እየታየ ነው፡፡ ለምሳሌ ሞያሌ የተደረገውን ውጊያ ማየት ይቻላል፡፡ይህ የጎሳ ግጭት ወይንም የቦረና ኦሮሞና የገሪ ሱማሌዎች ውጊያ አይደለም፡ ፡ምክንያቱም የሚጠቀሙበት መሳሪያና የውጊያው አይነት ፈጸሞ የጎሳ ግጭት አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ቤኒሻንጉል ጉሙዝም ተመሳሳይ ነው፡፡ ከዚህ አኳያሰላም የማስፈንና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ጉዳይ ውስጣዊ ስጋታችን ነው ሲሉ ይናገራሉ፡፡ይህን ስጋት ለማስወገድ ደግሞ ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ያለውን ሀይል አንስቶ ወደ ሌሎቹ የአገሪቱ ክፍል ማሰማራት እንደሚያስፈልግ የሚገልጹት ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ በኢትዮ-ኤርትራ ድንበር ሰፍሮ የነበረው ሰራዊት የማንቀሳቀስ ርምጃ ስጋት ሊፈጥር የቻለበት ምክንያት አንደኛው የኢትዮ-ኤርትራን ግንኙነት የተፈጠረውን ሰላም በመጠርጠር ሊሆን ይችላል፡፡ መነሻውም ‹‹በቀን እባብ ያየ ለሌት በቅርፊት ይሸሻል›› እንደሚባለው ተደጋጋሚ የሆነ አለመተማመኖች ስላሉ፣አሁንም ከኤርትራ በኩል ጦርነት ስለሚነሳብን ሰራዊቱ እዚህ አካባቢ መነሳት የለበትም ከሚል ቅን አስተሳሰብ የተነሳ ሊሆን ይችላል፡፡ሆኖም በአሁኑ ጊዜ ኤርትራ ኢትዮጵያን በጦርነት አትፈልጋትም ነው ያሉት፡፡ምክንያቱም ኢትዮጵያና ኤርትራ የሰላማቸውን ዋጋ ገና እያጣጣሙት ነው፡፡ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱም ተጧጡፏል፡፡ሌላው ኤርትራ ሰላም እየፈጠረች ያለችው ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ከጂቡቲና ከሶማሊያም ጭምር ነው፡፡ በኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲነሳም ኢትዮጵያ ጉልህ ሚና ተጫውታለች ሲሉ ነው ኤርትራ የኢትዮጵያ ስጋት አለመሆኗን ያስረዱት፡፡ሁለተኛው ምክንያት ግን ሰራዊቱ ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል መንቀሳቀስ የለበትም የሚሉት ወገኖች የራሳቸውን ድብቅ ፍላጎት ሊያስፈጸሙ በማሰብ ነው ይላሉ ሌተናል ጄነራል ባጫ፤ እዚህም እዚያ ብሄር ብሄረሰቦችን ለማጋጨት የሚፈልጉ ሰዎች ሰራዊቱ ወደ ሌሎች አገሪቱ ክፍሎች የሚንቀሳቀስ ከሆነ የማጋጨት ዕድሉ አይኖራቸውም፡፡ ከዚህ ተነስተው ሰራዊቱ መነሳት የለበትም ሊሉ ይችላሉ፡፡ስጋቱ ከማንኛውም ሆነ ከየትኛውም ወገን ይነሳ ሰራዊቱን የማንቀሳቀሱ ውሳኔው ግን በጣም ትክክለኛና አገራችን ውስጥ ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ የተወሰደ ዕርምጃ በመሆኑ ማንንም ስጋት ውስጥ የሚጥል አይደለም በሚል ሃሳብ አላቸው፡፡‹‹የመከላከያ ሰራዊት ትግራይ ላይ የሰፈረው ድንበሩን እንጂ ማንኛውንም የፖለቲካ ፓርቲ ለመጠበቅ አይደለም›› ያሉት ሌተናል ጄነራሉ፣ሰራዊቱን ስጋት ወደ አለባቸው አካባቢ አስገብቶ ሰላም እንዲያመጣ ማሰማራት ተገቢና ኃላፊነት የተሞላበት ርምጃ ነው፡፡እንዲያውም ዘግይቷል ብለዋል፡፡ሚያዝያ 28 ቀን 1990 ዓ.ም  የተቀሰቀሰው የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጦርነት ተከትሎ ሰራዊቱ ላለፉት 20 ዓመታት ያህል በድንበር አካባቢ ሰፍሮ ቆይቷል። አሁን የሁለቱ አገሮች መሪዎች የፈጠሩት ግንኙነት በስጋት ተወጥሮ የነበረው አካባቢ እፎይታ አግኝቷል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2011በጌትነት ምህረቴ", "passage_id": "437ceb6f74fdd9d260e62fb87249b701" }, { "passage": "የሱዳን የጦር ሰራዊት ሰራዊቱን በሚሳደቡ ጋዜጠኞችና የለውጥ እንቅስቃሴ መሪዎች ( አክቲቪስቶች ) ላይ ህጋዊ ርምጃ እንወስዳለን ሲል ተናገረ\nየጦር ኃይሉ ትናንት ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ በአገር ውስጥም ይሁን በውጭ ባሉ ጋዜጠኞች አክቲቪስቶች እና ሊሎችም የሚወሰድ የህግ ርምጃ ይኖራል፤ ይህኑ የሚያስፈጽም በሳይበር ወንጀሎች (በኢንተርኔት አማካይነት በሚፈጸሙ ወንጀሎች) ጉዳይ ልዩ ስልጠና ያለው መኮንን ሰይመናል ብሏል", "passage_id": "407af43b938c36ed8210bdffb7fe3a72" } ]
348e20b2a75919c8d8ad35e513ddf392
fa3b2da7adfb2e87723b00e9316e3be8
ማራቶንን በተፈጥሯዊ መንገድ ከ2 ሰዓት በታች የመሮጥ ውጥንነው፡፡
ነገር ግን የድል ዜናው ቦታውን ቀይሮ በተገናኙባቸው ውድድሮች ኬንያዊው አትሌት የርቀቱ ፈጣን ተሰኘ፡፡ በጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቆ የቆየው የሃገር አቋራጭ ንጉሱ ቀነኒሳም በርቀቱ ያለውን ተስፋ ከማሳየት በቀር ለሁለት ዓመታት ውጤት አላስመዘገበም ነበር፡፡ እአአ 2016 ግን የፓሪስ ማራቶንን በማሸነፍ በጠባብ የደቂቃዎች ልዩነት ሁለተኛው የርቀቱ ፈጣን አትሌት ለመሆን ችሏል፡፡ በቀጣዩ ዓመት በለንደን ማራቶን ያስመዘገበው ሰዓት ከፈጣኑ የዘገየ መሆኑ በርቀቱ ያለውን ተስፋ አጠራጣሪ አድርጎት ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በ5 እና 10ሺ ሜትር የሶስት ጊዜ የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑ ቀነኒሳ የባት ፣ የቁርጭምጭሚት፣ ተረከዝ፣ ሽንጥ እና ቋንጃ ጉዳቶች ጋር ትግል ሲያደርግ በመቆየቱ ነው፡፡ የአትሌቱ የረጅም ጊዜ ማኔጀር ጆስ ሄርሜንስም ስለ ቀነኒሳ ከሰሞኑ በዓለም አትሌቲክስ ድረ ገጽ አጠቃላይ መረጃ ሰጥቷል፡፡ አሰልጣኙ አትሌቱ የነበረበትን ሁኔታ ሲገልጽም ‹‹በአዲስ አበባ ያለው ህይወቱ ውጥረት የበዛበት በመሆኑ ለልምምድ እንዲሁም ለማገገም የተመቸ ጊዜ የለውም፡፡ ከሩጫው ባሻገር በቢዝነስ ስራዎችም ላይ ተሳታፊ እና የልጆች አባት እንደመሆኑም አብዛኛውን ጊዜውን በዚህ ያሳልፋል፡፡ በዚህ ሂደትም ጊዜውን ያለእረፍት እያሳለፈ ነበር›› ሲልም ይገልጻል፡፡ ‹‹የማራቶን ሁለተኛውን ሰዓት ካስመዘገበበት የበርሊን ማራቶን ሁለት ወራት አስቀድሞም ለጥቂት ጊዜ ከውጥረት መላቀቅ እንዳለበትና ጥሩ የማገገሚያ ጊዜ እንደሚኖረው አስረዳነው›› ይላል ማኔጀሩ፡፡ ይህን ማሳመን ቀላል ባይሆንም በመጨረሻ ግን ከቤተሰቦቹ ተለይቶ ለሁለት ወራት በሆላንድ በምትገኝ አንዲት ከተማ ለማሳለፍ የግድ ሆነ፡፡ አትሌቱም የሩጫ ህይወቱን ከማቋረጡ አስቀድሞ በማራቶን አንድ ታሪክ ማስመዝገብ የሚፈልግ በመሆኑ ከጉዳቱ በቶሎ አገግሞ ወደ ልምምድ እንዲገባ የቻሉትን ሁሉ ማድረጋቸውን ማኔጀሩ ያስታውሳል፡፡ ክብደቱ በመጨመሩም በሆላንዳዊው የስነ ምግብ ፕሮፌሰር አርማንድ ቤቶንቬል እገዛ የአመጋገብ ሁኔታውን ማስተካከል ተችሏል፡፡ በአዲስ አበባ ቆይታው የአመጋገብ ሁኔታው የተጠና አልነበረም፤ አብዛኛውን ጊዜ የሆቴል ምግብ የሚያዘወትር ከመሆኑ ጋር በተያያዘ እንደ አትሌት በሚጠበቅበት ሁኔታ ላይ አልነበረም፡፡ በባለሙያዎቹ አማካኝነትም ፕሮቲን፣ ሩዝ እና ድንች በተሻለ ሁኔታ እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ ስልጠናውንም በአግባቡ ነበር የሚከታተለው፡፡ ወደ ዋናው ስልጠና ከገባም በኃላ በሳምንት እስከ 50 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ጥሩ የሚባል ጊዜ አሳልፏል፡፡ የመልካም አስተሳሰብ ባለቤት በመሆኑም ከታሰበው በተሻለ ፍጥነት መሻሻል ሊያሳይ ችሏል፡፡ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኃላም በአሰልጣኝ ሃጂ አዲሎ ስር በመሆን ስልጠናውን ሳያዘባ ሲሰራ ስለ ነበር በጥቂት ጊዜ ወደ ቀደመ አቋሙ ሊመለስ ችሏል፡፡ ዝግጅቱ በርቀቱ ከፈጣኖች ተርታ ከሚሰለፈውና ከዓለም ቻምፒዮኑ አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ ጋር መሆኑም የተሻለ ነገር አስገኝቶለታል የሚል እምነት እንዳላቸው ኸርሜንስ ይናገራሉ፡፡ በእርግጥ ስልጠናውን በሚያደርግበት ወቅት አዲስ አበባ ዝናባማ የአየር ሁኔታ ነበራት፤ ይህም አስቸጋሪ ስለነበር ስልጠናውን በበፊቱ ልክ ማከናወን አንዳልተቻለም አልዘነጉም፡፡ ‹‹ውድድሩ ሲቃረብም በአትሌቱ ብቃት ሁላችንም ከመተማመን ላይ ደርሰን ነበር፡፡ እኛ በስልጠናው ወቅት ሲያሳይ በቆየው ብቃት ከፍተኛ ተስፋ ስንሰንቅ እርሱ ደግሞ በጥሩ ውጤት ማጠናቀቅን አላማው አድጎ ነበር፡፡ ከሚታመነው በላይ ጠንካራ አትሌት ነው፤ በውድድሩ ላይ ኬንያዊው አትሌት ከያዘው ክብረወሰን በሁለት ሰከንዶች ብቻ ዘግይቶ ገብቷል›› በማት አ ድ ና ቆ ታ ቸ ው ን ይገልፃሉ፡፡ እውቅና ያልተሰጠውና ሰው ሰራሽ በሆነ መንገድ ቢሆንም የሰው ልጁ 42ኪሎ ሜትሮችን ከ2ሰዓት በታች መግባት ይችላል የሚለው ሙከራ በኬንያዊው ኪፕቾጌ እውን ከተደረገ በኃላም የስፖርት ቤተሰቡ ጥያቄ ተመሳሳይ ሆኗል፡፡ ‹‹ቀጣዩ ምንድነው?›› የሚለው ፤ ምላሹም ቀነኒሳን ከማየት የተሻለ አለመኖሩን የሚያሳይ ነው፡፡ ቀነኒሳ ማራቶንን በተለመደው መንገድ ሮጦ በቴክኖሎጂ ሳይታገዝ ከ2፡00 በታች መሮጥ እንደሚችል በቅርቡ አብሮ እየሰራ የሚገኘው አሰልጣኙ ሃጂ አዲሎም በቅዳሜው እለት እትማችን ባደረጉት ቃለ ምልልስ መግለፃቸው ይታወቃል፡፡ አሰልጣኙ ሃጂም ‹‹ ቀነኒሳ ሩጫ ከማቆሙ አስቀድሞ ማራቶንን ከ2፡00 በታች ይሮጣል፣ በየትኛው ውድድር እንደሚሆን ግን መናገር አይቻልም›› ይላሉ፡፡ ቀነኒሳ ምናልባትም ይህን ለማሳካት የቀጣዩን ዓመት የበርሊን ማራቶን መታገስ ላይጠበቅበት ይችላል፡፡ በቀጣዩ ሚያዝያ በለንደን ማራቶን ለመሳተፍ በሆላንድ አገር የሚያደርገው ዝግጅት በታሰበው ልክ ከሄደ ህልሙን በቅርቡ እውን ሊያደርግ እንደሚችል ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 15/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23109
[ { "passage": "የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ ከሰጣቸው ታላላቅ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች አንዱ የሆነው የፎኮካ ማራቶን ከሳምንት በኋላ በጃፓን ይካሄዳል፡፡ በዚህ ውድድር የሚፎካከሩ የዓለማችን ጠንካራ አትሌቶች ስም ከወዲሁ ይፋ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን፤ የርቀቱ ኮከቦች የሆኑት ምሥራቅ አፍሪካውያን አትሌቶች የተለመደ የአሸናፊነት ግምት ተችሯቸዋል፡፡እኤአ በ2015 የቤጂንግ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በማራቶን ተከታትለው በመግባት የወርቅና የብር ሜዳሊያ ማጥለቅ የቻሉት ኤርትራዊው ግርማይ ገብረሥላሴና ኢትዮጵያዊው የማነ ፀጋዬ ትልቅ የአሸናፊነት ግምት ከተሰጣቸው አትሌቶች ግንባር ቀደም ናቸው፡፡ግርማይ ገብረሥላሴ በዓለም ቻምፒዮናው በአስራ ስምንት ዓመቱ ሳይጠበቅ ለታላቅ ድል በመብቃት ለኤርትራ በመድረኩ የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ ማጥለቁ የሚታወስ ሲሆን፤ በአንፃሩ በርቀቱ የተሻለ ልምድ የነበረው የማነ የብር ሜዳሊውን ለኢትዮጵያ ማስመዝገቡ አይዘነጋም፡፡ ሁለቱ የማራቶን ፈርጦች ከዓለም ቻምፒዮናው በኋላ በትልቅ ውድድር ዳግም ፎኮካ ማራቶን ላይ የሚያደርጉት ፉክክር የሚጠበቅ ይሆናል፡፡የማነ በበርካታ የማራቶን ውድድሮች በማሸነፍ ስማቸው ከሚጠቀስ የዓለማችን ድንቅ የማራቶን አትሌቶች አንዱ ሲሆን፤ ከሁለት ዓመት በፊት በዚሁ በፎኮካ ማራቶን 2:08:48 ሰዓት ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ይህም ሰዓቱ እኤአ 2012 ላይ በሮተርዳም ማራቶን ሲያሸንፍ ካስመዘገበው የራሱ ምርጥ ሰዓት በአራት ደቂቃ የተሻለ ሆኖ ተመዝግቦለታል፡፡ የማነ በዓለም ቻምፒዮናው የብር ሜዳሊያውን ካጠለቀ ወዲህ ጉልበቱ ላይ በገጠመው ጉዳት የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክን ጨምሮ በርካታ ውድድሮች ያመለጡት ሲሆን፤ ያለፈውንም ዓመት በጥሩ አቋም ላይ አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ በ2018 ወደ ጥሩ አቋም መመለሱን ባለፈው ሰኔ ወር የኦታዋ ማራቶንን 2:08:52 በሆነ ሰዓት በማሸነፍ አሳይቷል፡፡ግርማይ ገብረሥላሴ በበኩሉ ከዓለም ቻምፒዮናው ድሉ በኋላ በሪዮ ኦሊምፒክ ሌላ ታሪክ ይሠራል ተብሎ ሲጠበቅ ሜዳሊያ ውስጥ መግባት ሳይችል ቀርቷል፡፡ ይሁን እንጂ በዚህ ታላቅ መድረክ አራተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ እንደ ወጣት አትሌት መጥፎ የሚባል አልነበረም፡፡ከኦሊምፒኩ ስድስት ሳምንታት በኋላ በጠንካራው የኒውዮርክ ማራቶን ዳግም ሳይጠበቅ ለድል የበቃው ግርማይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ስሙን በርቀቱ ማግነን ችላል፡፡ 2:07:46 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያለው ግርማይ ባለፉት ሁለት ውድድሮቹ አቋርጦ መውጣቱ ምናልባትም ወደ ጥሩ አቋሙ ካልተመለሰ በዘንድሮው የፎኮካ ማራቶን ከየማነ ጋር የሚጠበቀውን ጠንካራ ፉክክር እንዳያሳይ ስጋት ሊሆን ይችላል፡፡በዚህ ውድድር የማነ ከግርማይ ባሻገር ከሌላ አትሌት ጠንካራ ፉክክር እንደሚገ ጥመው ይጠበቃል፡፡ ይህም ውድድሩ ላይ ከየማነ ቀጥሎ ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ይዞ የሚወዳደረው ኬንያዊው ቪንሰንት ኪፕሩቶ ሲሆን፤ በርቀቱ 2:05:13 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያለው አትሌት ነው፡፡\nበሌላ በኩል በዘንድሮው የፎኮካ ማራቶን ትኩረት ሳይሰጠው መታለፍ የሌለበት አትሌት ጃፓናዊው ዩኪ ካዉቺ ነው፡፡ ይህ አትሌት ካለፉት ዘጠኝ የፎኮካ ማራቶን ውድድሮች በስምንቱ ላይ በመሳተፍ ከሌሎቹ አትሌቶች የተሻለ ልምድ ማካበት ችሏል፡፡ ዩኪ ልምድ ማካበቱ ብቻ በውድድሩ አስፈሪ ወይንም ጠንካራ ተፎካካሪ ባያደርገውም በርቀቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያስመዘገበ ያለው ውጤትና ጥሩ አቀም ለምሥራቅ አፍሪካውያኑ አትሌቶች አስፈሪ ያደርገዋል፡፡ ዩኪ በዚህ ውድድር እኤአ በ2011፣2013እና 2016 ሦስተኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ በሦስቱም ውድድሮች ርቀቱን ከ2፡10 ሰዓት በታች በማጠናቀቅ ጥንካሬውን ማሳየት ችላል፡፡ ዩኪ ምሥራቅ አፍሪካውያን ደጋግመው ያሸነፉትን የቦስተን ማራቶን በቅርቡ ማሸነፉም በአገሩና በደጋፊዎቹ ፊት በሚያደርገው ውድድር ቀላል ግምት እንዳይሰጠው ያደርጋል፡፡", "passage_id": "ba0a2da0290d0ea00dd0d72866a0b83f" }, { "passage": "ኤሉድ ኪፕቾጌን ለማሸነፍ እንዴት ያለ ወኔ ይበቃ ይሆን? ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች የሮጠውን ብርቱ አትሌት ለማሸነፍ ምን ሲደረግ ይቻላል?ጥብቅ ልምምድ ወይስ ተሰጥኦ? ለለንደን ማራቶን አሸናፊው ሹራ ቂጣታ ግን ጥሩ ቁርስ በቂ ነው።ባለፈው ዓመት በዩኬ ዋና ከተማ አራተኛ በመሆን ነው ያጠናቀቀው። ያኔ ኬኒያዊው ኪፕቾጌ ነው ያሸነፈው። በወቅቱ ሹራ በትዊተር ሰሌዳው ላይ ባዶ ሆዱን መሮጡን፣ ለቁርስ ፍራፍሬ ብቻ መመገቡን ገልጾ ነበር።ሹራ በወቅቱ 35 ኪሎ ሜትሮች ከሮጠ በኋላ የተሰማውን ሲያሰፍር \"ሆዴ ከጀርባዬ ጋር የተጣበቀ መስሎኝ ነበር፤ ሞርሙሮኝ ነበር\" ብሏል።በዚህ ዓመት ከስህተቱ የተማረው ሹራ ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት ጥሩ ምግብ ወሳስዷል።ለቢቢሲ ስፖርት አፍሪካ \" ሁሉንም ነገር ተመግቤያለሁ\" ብሏል።\"ሾርባ፣ ዳቦ፣ እንቁላል እና እርጎ ወስጃለሁ፤ አቅም የሚሆነኝንና ውድድሩን በጥሩ ጉልበት መፎካከር የሚያስችለኝን ሁሉ ወስጃለሁ።\" ውድድሩ ደግሞ ከ2014 ጀምሮ በማራቶኑ መስክ አልበገር ያለውን ኬንያዊ ማንበርከክን ያካተተ ነበር። ኪፕቾጌ የዋዛ አትሌት አይደለም። በኦሎምፒክ መንደር ስሙ በደማቅ ተጽፏል። የዓለም ክብረ ወሰን በእጁ ነው።የ35 ዓመቱ ኪፕቾጌ በለንደን ለአምስተኛ ጊዜ ድልን ለመቀዳጀት ጉልበቱን አበርትቶ ሞራሉን አደርጅቶ ነው የተገኘው።የዓለም መገናኛ ብዙኃንም ስሙን ደጋግመው ያነሳሉ። ምስሉን ደጋግመው ያሳያሉ። ጋዜጦች የፊት ገጻቸው ላይ አትመውታል።ለንደን ለኪፕቾጌ፣ ኪፕቾጌም ለለንደን መሃላ ያላቸው ይመስላል።ኪፕቾጌና ለንደን ግን ያላቸው ቃል ኪዳን ፈረሰ። መፍረስ ብቻ ሳይሆን ስምንተኛ ወጣ። ከፊት የፈለጉት ከኋላ አገኙት። በኋላም ጆሮውን አሞት እንደነበር አስረዳ።ለረዥም ርቀት ሩጫ እርጥበታማ አየርና ቅዝቃዜ ምቹ አይደለም።ሹራ የገባበት ሰዓትም፣ ሁለት ሰዓት ከአምስት ደቂቃ ከ41 ሰከንድ የሚያሳየው ይህንኑ ነው። ሹራ ግን እንደውም አየሩ ረድቶኛል ሲል ያምናል።እኤአ ከ2013 ወዲህ የለንደን ማራቶንን ሲያሸንፍ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የሆነው ሹራ \"ሲዘንብ በጣም ደስ አለኝ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በከባድ ዝናብ ውስጥ ነው ልምምድ ስሰራ የነበረው\" ይላል። \"አንድ ቀን ሶደሬ ለልምምድ ሄድኩኝ፣ ከባድ ዝናብ እየዘነበ ከተማው በጎርፍ ተጥለቅልቋል። አሰልጣኜ እኔን ለማዳን መምጣት ሁሉ ነበረበት\" ሲል የነበረውን የልምምድ ሁኔታም ያስታውሳል።\"የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሲከሰት፣ ቤት አልተቀመጥኩም። ለአምስት ወራት ያህል ከአሰልጣኜ ጋር ልምምድ ስሰራ ነበር። ይህን ድል ኪፕቾጌን ማሸነፌ ልዩ አያደርገውም፤ ጠንክሬ መስራቴ ነው ልዩ የሚያደርገው።\" ቀነኒሳ በቀለ ባጋጠመው ጉዳት የተነሳ ከውድድሩ መውጣቱን ካሳወቀ በኋላ በኪፕቾጌና በቀነኒሳ መካከል ይኖራል ተብሎ የታሰበው ፍልሚያ ሳይሳካ ቀረ።ስለዚህ ማንም የቀነኒሳን አገር ልጅ፣ ሹራን ከኪፕቾጌ ጋር አነጻጽሮ ለማወዳደርና የዜና ፍጆታ ለማድረግ ፍላጎት አላሳየም።ሹራም ቢሆን \"ሁሉም ትኩረቱ የነበረው ኪፕቾጌ እና ቀነኒሳ ላይ ነበር፤ እኔን ዞርም ብሎ ያየኝ አልነበረም\" ሲል ይገልጻል።\"ለራሴ ለዓለም ሌላ ሻምፒዮን መኖሩን አሳያለሁ ብዬ ነገርኩት፤ እናም ይህ ስሜት ነው እስከመጨረሻው ድረስ በራስ መተማመንና በሙሉ አቅም እንድቀጥል የረዳኝ።\"ሹራ በበርካታ የስፖርቱ አድናቂዎች ዘንድ የሚታወቅ ስም አይደለም። ነገር ግን በለንደን ሁለት ጊዜ ሁለተኛ ሆኖ አጠናቅቋል፣ በ2018 ደግሞ በኒውዮርክ ሁለት ሰዓት ከአራት ደቂቃ ከ49 ሰከንድ በመግባት የራሱን ምርጥ ሰዓት አስመዝግቧል። በዙሪያው ያሉ አትሌቶች የ24 ዓመቱን ሹራ ዝምተኛ ግን በራስ መተማመን ያለው ሲሉ ይገልፁታል።የሹራ ወኪል ሁሴን ማኬ ለቢቢሲ ስፖርት አፍሪካ፤ \" በጣም መልካም፣ የሚፈልገውን የሚያውቅ፣ ቤተሰቡን የሚያስቀድም ሰው ነው። እናም የእርሱ ምርጥ ነገሩ በራስ መተማመኑ ነው\" ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል።\"በለንደን በራሱ በብርቱ ተማምኖ ነበር፤ እናም ወደ ውድድር ሲገባ ውድድሩ ውስጥ ስላሉት አትሌቶች ግድ አልሰጠውም፤ ያም አሁን ላገኘው ሻምፒዮናነት ረድቶታል። ተስፋ አደርጋለሁ በዚሁ ይቀጥላል።\" ሹራ አትሌቲክስን የተዋወቀው በትምህርት ቤት ውስጥ ነው። ኋላም እኤአ ከ2015 ጀምሮ አሰልጣኝ ሃጂ አዲሎ በአዲስ አበባ እያሰለጠኑት ይገኛሉ።\"በጣም ደፋር አትሌት ነው፤ እናም ሁልጊዜ አቅሙን እስከቻለ ድረስ ይጠቀማል\" ይላሉ አሰልጣኙ። አሰልጣኝ ሃጂ ወደ እንግሊዝ ለመሄድ ቀናት ሲቀራቸው የኮሮናቫይረስ እንዳለባቸው በምርመራ በመረጋገጡ ድሉን በአካል ተገኝተው ለማጣጣም አልታደሉም።ቢቢሲ ሹራን እንዴት ማሰልጠን እንደጀመሩ ሲጠይቃቸው \"ሹራ ከመጣበት አካባቢ የሆነ ሰው ከኔ ጋር አብሮ ይሮጥ ነበር። እናም እኔ ወዳለሁበት ካምፕ አምጥቶት እስቲ እየው አለኝ። ሞከርነው፤ ጥሩ ነበር ግን ፅናቱንና ፍጥነቱን ማሻሻል ነበረበት\" በማለት ሁኔታውን ያስታውሳሉ።\"በሶስት ወር ውስጥ፣ በጣም በርካታ ነገር አሻሻለ፤ እናም የመጀመሪያውን ማራቶን እንዲካፈል ወደ ሻንጋይ ላክነው።\" ሹራ የተገኘው ሰባት ልጆች ካሏቸው ገበሬ ቤተሰቦች ነው። \"ትምህርት በጣም እወድ ነበር፤ ዶክተር አልያም ፓይለት ነበር መሆን የምፈልገው። ነገር ግን ከድሃ ቤተሰብ ስለሆነ የተገኘሁት ቤተሰቦቼን ለመርዳት ትምህርቴን ማቋረጥ ነበረብኝ\" በማለት ልጅነቱን ያስታውሳል።\"አንድ ቀን ዝነኛ እሆናለሁ፤ አለምን እዞራለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም\" በማለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ስለ እርሱ እና ስለድሉ በትዊተር ሰሌዳቸው ለመጀመሪያ ጊዜ መጻፋቸውን በመግለጽ፤ \"አስቤ የማላውቀውን ህይወት ነው እየኖርኩ ያለሁት\" ይላል።የሁለት ልጆች አባት የሆነው ሹራ ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ በወንዶች ማራቶን ለሁለት አስርታት ያጣችውን ድል መመለስ ይፈልጋል።\"ለአገሬ እና ለልጆቼ ጥሩ ትዝታ እንዲሆን የወርቅ ሜዳሊያ ማምጣት እፈልጋለሁ። ከዚያም 'አባታችን የኦሎምፒክ ሜዳሊያ አሸናፊ ነው' ይላሉ።\"", "passage_id": "a4ae53d48b1f51c07345d4acf7df91af" }, { "passage": "ያለፈው ሳምንት በአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ ታላላቅ ውድድሮች የተስተናገዱበት ሆኖ አልፏል። ከቤት ውስጥ በርካታ ውድድሮች አንስቶ እስከተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮችም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በድል ተንቆጥቁጠው ታይተዋል። ከጣፋጭ ድሎቻቸው ባሻገርም በተለያዩ ርቀቶች ፈጣን ሰዓቶችና ክብረወሰኖች ማስመዝገብ ችለዋል። ትናንት ማለዳ በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ በተካሄደው የራስ አል ኪማህ ግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን ያስመዘገቡት ውጤት በጉልህ የሚጠቀስ ሲሆን በሁለቱም ፆታ ፈጣን ሰዓቶች ተመዝግቦበታል። በሴቶች መካከል በተካሄደው ውድድር ሰንበሬ ተፈሪ በርቀቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳትፋ 1፡05፡45 በሆነ ሰዓት አሸናፊ ሆናለች። ይህም በታሪክ በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎ የተመዘገበ ፈጣን ሰዓት ሲሆን የኢትዮጵያ ክብረወሰን ሆኖ ሊመዘገብም ችሏል። እጅግ ጠንካራ ፉክክር በታየበት ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ አራት ባለው ደረጃ ውስጥ ሲያጠናቅቁ የዓለም ግማሽ ማራቶን የክብረወሰን ባለቤት የሆነችው ነፃነት ጉደታ እስከ መጨረሻ ድረስ ታግላ ለጥቂት በመቀደሟ በተመሳሳይ ሰዓት ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ዘይነባ ይመር 1:05:46 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ሆና ስትፈፅም ደጊቱ አዝመራው በ1:06:07 ሰዓት ተከታዩን ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በዚህ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች እስከ መጨረሻ ያደረጉት አጓጊ ፉክክር ከአንድ እስከ ሦስት ባለው ደረጃ ያጠናቀቁ አትሌቶች የገቡበት ሰዓት ልዩነት የአንድ ሰከንድ ብቻ እንዲሆን አድርጎታል። በተመሳሳይ በወንዶች መካከል በተካሄደው ውድድር ለድል ሲጠበቁ የነበሩ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ቀዳሚውን ደረጃ በኬንያዊው ስቲፈን ኪፕሮፕ ቢነጠቁም ሁለተኛና ሦስተኛ ሆነው አጠናቀዋል። የአሸናፊነት ግምት ተሰጥቶት የነበረው አባዲ ሃዲስ ድንቅ ፉክክር ቢያሳይም በአጨራረስ ድክመት ኪፕሮፕ በሁለት ሰከንድ 58፡42 በሆነ ሰዓት ቀዳሚ መሆን ችሏል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ፍቃዱ ሃፍቱ 59:08 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ሆኖ ውድድሩን ጨርሷል። ኪፕሮፕ ያስመዘገበው ሰዓት የውድድሩ ክብረወሰን ከነበረው ሰዓት ጋር እኩል ሲሆን በርቀቱም በታሪክ አምስተኛው ፈጣን ሰዓት መሆን ችሏል። ካለፈው ረቡዕ አንስቶ በተለያዩ የዓለማችን ከተሞች ሲካሄድ በነበረው የቤት ውስጥ የዙር ውድድርም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አስደናቂ ውጤት አስመዝግበዋል። ፖላንድ ቶሩን በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮኑ ወጣት አትሌት ሳሙዔል ተፈራ የውድድር ዓመቱን መሪ ሰዓት3:35.57 በማስመዝገብ አሸናፊ ሆኗል። በዚህ ውድድር ልምድ ያለው ኢትዮጵያዊ አትሌት አማን ወጤ እልህ አስጨራሽ ፉክክር ቢያደርግም በመጨረሻዎቹ ሦስት መቶ ሜትሮች የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ሳሙዔል ተፈራ እጅ የሚሰጥ አልነበረም። በተመሳሳይ ቀንና ቦታ በሴቶች ስምንት መቶ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሃብታም አለሙ በፈጣን ሰዓት ታጅባ ያሸነፈችበት ክስተትም ያልተጠበቀ ነበር። አትሌት ሃብታም አለሙ በርቀቱ ከፍተኛ ልምድና ችሎታ ያላትን እንግሊዛዊቷን አትሌት ላውራ ሙዒርን ቀድማ በመግባት የውድድር ዓመቱ መሪ የሆነውን1:59.49 ሰዓት ማስመዝገብ ችላለች። በሳምንቱ ከተመዘገቡት ታላላቅ ውጤቶች አንዱ የሆነው በስፔን ሳባዴል በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር ገንዘቤ ዲባባ ያስመዘገበችው ነው። የዓለም የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ቻምፒዮንና የርቀቱ የቤት ውስጥም ከቤት ውጪም ክብረወሰን ባለቤቷ ገንዘቤ ዲባባ አሁንም በርቀቱ ከዓለማችን ኮከብ አትሌቶች አንዷ መሆኗን እያሳየች ትገኛለች። ገንዘቤ ምንም እንኳን ወጣ ገባ የሆነ አቋም በማሳየት ያለፈውን የውድድር ዓመት ጎልታ ባትታይም ዘንድሮ 3:59.08 የሆነ ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ሌላኛዋን ኢትዮጵያዊት አትሌት ለምለም ሃይሉን አስከትላ በመግባት ማሸነፍ ችላለች። አዲስ ዘመን የካቲት 2/2011ቦጋለ አበበ ", "passage_id": "50d23e6f5e2cf38f78d5c113c96dbab4" }, { "passage": "በእስያ አህጉር ትልቁ የጎዳና ላይ ሩጫ የፈረንጆቹ ዓመት በገባ የመጀመሪያው ወር ሦስተኛው እሁድ ይካሄዳል። በአህጉሪቷ በርካታ ሯጮችን አሳትፎ የሚካሄደው ውድድር 45ሺ የአሜሪካ ዶላር ሽልማትን በማሳፈስም ቀዳሚው ነው። በለንደን ማራቶን በመነሳሳት እአአ 2004 ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው የሙምባይ ማራቶን በቀጣዩ ዓመት ከዓለም ታላላቅ የጎዳና ላይ ውድድሮች ተርታ ለመሰለፍ በቅቷል። በአጭር ጊዜ እድገት በማሳየቱም እአአ 2009 የብር ደረጃ ሲያገኝ፤ በቀጣዮቹ ዓመታት በወርቅ እና ብር ደረጃዎች ውድድሮችን ሲያካሂድ ቆይቶ ያለፈው ዓመት በድጋሚ የወርቅ ደረጃውን ተረክቧል። ሕንድ ስሟን በምታስጠራበት ዓመታዊው የማራቶን ውድድር ላይም ታላላቅ የቦሊውድ ተዋናዮች፣ የንግድ ሰዎች፣ ጎብኚዎችና የሀገሬው ዜጋ ሲሳተፉ፤ ታዋቂና ዝነኛ አትሌቶችም ይፋለሙበታል።በዚህ ዓመቱ ውድድር ላይም እንደተለመደው ተሳታፊነታቸውን ያረጋገጡት ኬንያውያንና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአሸናፊነት ቅድመ ግምቱን አግኝተዋል። በሴቶች በኩል በሚካሄደው ውድድር የአምናዋ አሸናፊ ወርቅነሽ አለሙ በድጋሚ የቦታውን ክብር ትቀዳጃለች በሚል ይገመታል። ከ2:28:00 በታች የሆነ ፈጣን ሰዓት ካላቸው ስምንት አትሌቶች መካከል አንዷ የሆነችው አትሌቷ ባለፈው ዓመት የገባችበት\n2:25:25 የሆነ ሰዓት በሙምባይ ማራቶን ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ነው። በዚሁ ዓመት በአምስተርዳም ማራቶን የተሳተፈችው አትሌቷ ስድስተኛ ደረጃን በመያዝ ታጠናቅ እንጂ ያስመዘገበችው 2:24:42 የሆነ ፈጣን ሰዓት ነው። በወንዶች ምድብ ደግሞ ኬንያዊው ኮስማስ ላጋት የሙምባይ ማራቶንን ለሁለተኛ ጊዜ አሸናፊ እንደሚሆን ይጠበቃል። ባለፈው ዓመት በዚህ ውድድር ላይ የተካፈለው ላጋት ከ29ኪሎ ሜትር በኋላ ያሉትን ርቀቶች ከሌሎች ተነጥሎ ብቻውን በመሮጥ ነበር ለአሸናፊነት የበቃው፤ የርቀቱን የመጨረሻ መስመር ለመርገጥ የፈጀበት ጊዜም 2:09:15 ነበር። አትሌቱ በዚህ ውድድር ላይ ከአሸናፊነት ባለፈ እአአ 2016 በሀገሩ ልጅ የተመዘገበውን ክብረወሰን በማሻሻልም ጭምር 15ሺ የአሜሪካ ዶላር ማበረታቻውንም ለመውሰድ አቅዷል። አትሌቱ በሰጠው አስተያየትም፤ አምና የዚህ ውድድር አሸናፊ መሆኑ ለዚህ ዓመት ሊረዳው የሚችል ልምድ እንዳስገኘለትና የመጀመሪያውን ግማሽ በፍጥነት በመሮጥ ሰዓት ለማሻሻል ማቀዱን ነው የገለጸው።አዲስ ዘመን\nጥር\n2/2012 ዓ.ም ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "a13550c94ac8c2abddd3ebc9ec5ed107" }, { "passage": "ቀነኒሳ በቀለ ከማራቶን ክብረ ወሰን ቀጥሎ ሁለተኛው ምርጥ ሰዓት ነው በተባለ 2 ሰዓት ከአንድ ደቂቃ ከአርባ አንድ ሰከንድ በማስመዝገብ ነው የበርሊን ማራቶንን ማሸነፍ የቻለው።\n\nቀነኒሳ ከውድድሩ በኋላ ለቢቢሲ እንደተናገረው የዚህን ውድድር ውጤት \"ከሞት እንደመነሳት ነው የምመለከተው\" ሲል ጠቅሶ ምክንያቱንም ሲያስረዳ ለረጅም ጊዜ በህመም ምክንያት ከሩጫ ውድድር እርቆ መቆየቱን ይገልጻል። \n\n• በወለደች በ30 ደቂቃ ውስጥ የተፈተነችው ተማሪ ስንት አስመዘገበች?\n\n• በዶሃ የሴቶች ማራቶን ሦስት ኢትዮጵያውያን ሯጮች አቋርጠው ወጡ \n\nበቀጣይ በጤናው ላይ ምንም ችግር ካላጋጠመው የዓለም የማራቶን ክብረ ወሰንን ለመስበር እንደሚሰራ ተናግሯል።\n\n\"ህመም ላይ ስለነበርኩ ክብረወሰኑን ለመስበር የሚያስችል በቂ ልምምድ አላደረግኩም\" የሚለው ቀነኒሳ ለዚህ ውጤት ያልተቋረጠ የወራት ልምምድ እንደሚያስፈልግ ጠቅሶ \"በቅርቡ የማራቶን ክብረ ወሰን ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳል\" ሲል ተናግሯል። \n\nበሴቶቹ የማራቶን ውድድር አንደኛና ሁለተኛ በመውጣት ኢትዮጵያዊያን ያሸነፉ ሲሆን አንደኛ አሸቴ በከሬ ሁለተኛ ማሬ ዲባባ በመሆን ተከታትለው አሸናፊነቱን ተቆጣጥረውታል። \n\n• በወለደች በ30 ደቂቃ ውስጥ የተፈተነችው ተማሪ ስንት አስመዘገበች?\n\nበወንዶቹ ውድድር በአንደኛነት ካሸነፈው ቀነኒሳ በቀለ በተጨማሪ ኢትዮጵያዊያኑ ብርሐኑ ለገሰ ሁለተኛ እንዲሁም ሲሳይ ለማ ሦስተኛ በመውጣት በሁለቱም ጾታዎች የበርሊን ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቋል። \n\nየ37 ዓመቱ ቀነኒሳ በቀለ ከዚህ በፊት በተካሄዱ የኦሊምፒክና የዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች ላይ በተከታታይ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ሲሆን ክብረ ወሰኖችንም ያሻሻለ ኮከብ አትሌት ነው።\n\nበኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ የተያዘው የማራቶን ክብረወሰን ላይ ለመድረስ ሁለት ሰከንዶችን ዘግይቶ ውድድሩን የጨረሰው ቀነኒሳ \"አዝናለሁ፤ እድለኛ አልነበርኩም። ነገር ግን ተስፋ አልቆርጥም፤ ክብረ ወሰኑንም ለመስበር እችላለሁ\" ሲል ከበርሊኑ ድሉ በኋላ ተናግሯል። \n\n ", "passage_id": "faff35d6b63feecb25c0cbc8fec0287c" } ]
381ab3999dd19cddfc26f2d9e264d750
32816ef5eb105c385ccff5fa9eb80d0d
ሉሲዎቹ ወደ አፍሪካ ዋንጫ የመመለስ ሰፊ እድል አላቸው
 የ2020 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያና ማጣሪያ ጨዋታዎች ድልድል ይፋ ተደርጓል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ሴት ብሔራዊ ቡድን (ሉሲዎቹ) በቅድመ ማጣሪያና ማጣሪያ ጨዋታዎች የሚገጥሙትን ቡድን አውቀዋል። ሉሲዎቹ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ከጅቡቲ ብሔራዊ ቡድን ጋር የፊታችን ሚያዚያ አራት ቀን የሚያደርጉ ሲሆን ጅቡቲን በደርሶ መልስ ጨዋታ ድምር ውጤት የሚያሸንፉ ከሆነ በመጨረሻው የማጣሪያ ጨዋታ ከሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚጫወቱ ይሆናል። በአሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው የሚመራው የኢትዮጵያ ሴት ብሔራዊ ቡድን ለ2020 የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከወዲሁ ለውድድሩ ትኩረት በመስጠት ከፍተኛ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ሲሆን አሰልጣኙ ቡድኑን ለአፍሪካ ዋንጫ ማሳለፍ ካልቻሉ ራሳቸውን ከአሰልጣኝነት ስራ እንደሚያገሉ መግለፃቸው ይታወሳል። ለመጀመሪያ ጊዜ ሰላሳ ሁለት አገራትን የሚያሳትፈው የ2020 የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ 2018 ተካሂዶ ከነበረው ውድድር አስራ ሁለት አገራትን ጨምሮ ሲካሄድ ዘንድሮ የመጀመሪያው ይሆናል። ይሁን እንጂ ይህን ውድድር የሚያዘጋጀው አገር እስካሁን አልታወቀም።ካፍ የ2020 የሴቶችን የአፍሪካ ዋንጫ ሞሮኮ እንድታዘጋጅ ፍላጎት እንዳለው የተለያየ መረጃ እየወጣ ይገኛል።ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከበጀት እጥረት ጋር ተያይዞ የ2020 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫን እንደማታዘጋጅ ከተገለጸ ወዲህ የአፍሪካ እግር ኳስን በበላይነት የሚመራው ካፍ ደቡብ አፍሪካ ውድድሩን እንድታዘጋጅ ጥሪ ቢያቀርብላትም ለ2023 የሴቶች ዓለም ዋንጫን ለማዘጋጀት ፉክክር ውስጥ በመግባቷና የዓለም ዋንጫውን ለማዘጋጀት ከፍተኛ ስራ ውስጥ በመገኘቷ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጓ ይታወቃል። ካፍ የ2020 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫን አዘጋጅነት ጥያቄ በቅርቡ የመላው የአፍሪካ ጨዋታዎችን በድምቀት ወደ አዘጋጀችው ሞሮኮ ፊቱን በማዞር ጥያቄ ሊያቀርብ እንደተዘጋጀ ታውቋል። ሞሮኮ የ2020 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫን የምታዘጋጅ ከሆነ ሉሲዎቹ ከጅቡቲ አቻቸው ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ የአፍሪካ ዋንጫ ትኬታቸውን በቀላሉ የሚቆርጡበት እድል ሰፊ ይሆናል። የጅቡቲ ብሔራዊ ቡድን ከአራት ሳምንት በፊት ተካሂዶ በነበረው የመካከለኛና ምስራቅ አፍሪካ(ሴካፋ) ዋንጫ ላይ ከዩጋንዳ፣ኬንያና ኢትዮጵያ ጋር ተደልድሎ በኬንያ 13ለ0፣ በዩጋንዳ 12ለ0 እንዲሁም በኢትዮጵያ 8 ለ 0 ተሸንፎ በውድድሩ በአጠቃላይ ሰላሳ አንድ ግቦች በማስተናገድ አንድም ግብ ሳያስቆጥር መቅረቱ ይታወሳል። ይህም ሉሲዎቹ በቅድመ ማጣሪያው ጨዋታ በቀላሉ አሸንፈው ወደ ቀጣዩ ማጣሪያ እንደሚያልፉ ከፍተኛ ግምት እንዲሰጣቸው አድርጓል። እኤአ 1991 ላይ በተጀመረው የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ላይ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 2002 ተሳታፊ መሆን ብትችልም በውድድሩ ከምድብ ጨዋታዎች ማለፍ እንዳልቻለች ይታወሳል። 2004 ላይ ዳግም ተሳታፊ በመሆን አራተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችበት ውጤት በታሪክ ትልቁ ሲሆን ለመጨረሻ ጊዜ በመድረኩ የተሳተፈችው 2012 ላይ ነው። ዘንድሮ ግን ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ መድረኩ የመመለስ ትልቅ ተስፋ ሰንቃለች።አዲስ ዘመን አርብ ህዳር 26/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23656
[ { "passage": "በጋና ለሚስተናግደው የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ማጣሪያ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የተገኘው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ምሽት ወደ አልጀርስ በካይሮ ትራንዚት በማድረግ ያመራል፡፡ ሉሲዎቹ ከአልጄሪያ ጋር ላለባቸው የድርሶ መልስ ጨዋታ ላለፈው አንድ ወር ዝግጅታቸውን ሲያከናውኑ የቆዩ ሲሆን ዛሬ አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ የመጨረሻ 18 ተጫዋቾችን ዝርዝር ይፋ አድርጋለች፡፡አሰልጣኝ ሰላም በዝግጅት ላይ ከነበሩ ተጫዋቾች መካከል አምስቱን ከአልጀርሱ ጨዋታ ውጪ ያደረገች ሲሆን አባይነሽ ኤርቄሎ፣ ፅዮን እስጢፋኖስ፣ በጉዳት ላይ የምትገኘው መስረም ካንኮ፣ ቤዛዊት ተስፋዬ እና ቤተልሔም ሰማን ወደ አልጄሪያ ከሚጓዘው ቡድን ውስጥ የተቀነሱ ናቸው፡፡የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ ጨዋታ የፊታችን ረቡዕ በስታደ ጁላይ 5 ምሽት 4 ሰዓት ላይ ሲደረግ ጨዋታውን የጋምቢያ አርቢትሮች ይመሩታል፡፡ ንግስት መዓዛ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) ፣ ታሪኳ በርገና (ጥረት)መሠሉ አበራ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ፣ ብዙዓየሁ ታደሰ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ፣ ቤተልሄም ከፍያለው (ኤሌክትሪክ) ፣ ታሪኳ ደቢሶ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) ፣ ገነሜ ወርቁ (ጌዴኦ ዲላ)ሠናይት ቦጋለ (ደደቢት) ፣ አረጋሽ ከልሳ (አካዳሚ) ፣ ዙሌይካ ጁሀድ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) ፣ ህይወት ደንጊሶ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) ፣ እመቤት አዲሱ (መከላከያ) ፣ አለምነሽ ገረመው (ኢትዮ ኤሌክትሪክ)ምርቃት ፈለቀ (ሀዋሳ ከተማ) ፣ ሎዛ አበራ (ደደቢት) ፣ ትዕግስት ዘውዴ (ደደቢት) ፣ ሴናፍ ዋቁማ (አዳማ ከተማ) ፣ ረሂማ ዘርጋ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)", "passage_id": "8c2366064ae0b5c7fcbbdb2e67ea074d" }, { "passage": "በፓናማ እና ኮስታሪካ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ቅድመ ማጣርያ የመጀመርያ ጨዋታቸውን ከቡሩንዲ ጋር ቅዳሜ ዕለት አድርገው በሰፊ የግብ ልዩነት ያሸነፉት ተተኪዎቹ ሉሲዎች ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል።በአሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል እና ህይወት አረፋይኔ እየተመራ ቡሩንዲ ኢኒዋሪ ስታዲየም ላይ 5-0 በማሸነፍ የቅድመ መጣሪያውን የመጀመሪያ ጨዋታ በድል የጀመረው ቡድኑ በኢትዮጽያን ሰዓት አቆጣጠር ማምሻውን 3:30 አዲስ አበባ የደረሰ ሲሆን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አብዱራዛቅ መሐመድ እንዲሁም የእግር ኳስ ልማት ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ገብረሥላሴ በስፍራው በመገኘት ለልዑካን ቡድኑ አቀባበል አድርገዋል። የእንኳን ደህና መጣቹ መልዕክት ከተላለፈ በኋላም ወደተዘጋጀላቸው ማረፊያ (ኢትዮጵያ ሆቴል) በቀጥታ አምርተዋል።ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከቡሩንዲ ጋር የሚያደርገው የመልስ ጨዋታን ጥር 24 የሚያከናውን ሲሆን ባህር ዳር ስታዲየም ጨዋታው የሚከናወንበት ቦታ ነው።", "passage_id": "ae85f49cbaf4c09e786742a58e12d2a2" }, { "passage": "የኢትዮጵያ\nሴቶች ብሔራዊ ቡድን እ.ኤ.አ በ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ ለመሳ ተፍ የመጀመርያ የማጣርያ ጨዋታውን የፊታችን መጋቢት 25 ከዩጋንዳ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ጋር በአዲስ አበባ ስታ ዲየም ያከናውናል። ብሔራዊ ቡድኑ ከፊት ለፊቱ ለሚጠብቀው የማጣሪያ ጨዋታ ከመጋቢት 12 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ልምምድ ያካሂዳል። የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ለማሰልጠን ባሳለፍነው ሳምንት ከስምምነት የደረሱት አሰልጣኝ ሠላም ዘርዓይ ብሔራዊ ቡድን ከፊቱ ለሚጠ ብቀው የኦሎምፒክ ማጣሪያ ጨዋታ ለ30 ተጫዋቾች የመጀመርያ ጥሪ አድርገዋል። በአሰልጣኝ\nሰላም ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ የመከላከያዋ ማርታ በቀለ፣ ታሪኳ በርገና ከጥረት ኮርፖሬት፣ ከሀዋሳ ከተማ አባይነሽ ኤርቄሉ እንዲሁም ምህረት ተሰማ ከጌዴኦ ዲላ እግር ኳስ ክለብ ናቸው። በተከላካይ ክፍል ከአዳማ ከነማ አራት ተጫዋቾች ጥሪ የተደረገላቸው ሲሆን መስከረም ካንኮ፣ እፀገነት ብዙነህ፣ ናርዶስ ዘውዴ፣ ነፃነት ፀጋዬ ናቸው። ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገነሜ ወርቁ፣ ታሪኳ ደቢሶ፣ ብዙዓየሁ ታደሠ ሲሆኑ ከመከላከያ መሠሉ አበራ፣ ከጥረት ኮርፖሬት አሳቤ ሙሶ፣ ትዕግስት ኃይሌ ደግሞ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። በአማካይ\nስፍራ ትዕግስት ያደታ፣ አሰልጣኝ ሠላም ዘርዓይ ብርቱካን ገብረክርስቶስና ሕይወት ዳንጊሶ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ ከመከላከያ እግር ኳስ ክለብ አረጋሽ ከልሳ እና እመቤት አዲሱ፤ ብርሃን ኃይለሥላሴ ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሰናይት ቦጋለ ከአዳማ ከተማ፣ ዓለምነሽ ገረመው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እንዲሁም ዮርዳኖስ ምዑዝ ከመቐለ 70 እንደርታ በምርጫው የተካተቱ ተጫዋቾች ሆነዋል። በአጥቂ ስፍራ ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ ረሃማ ዘርጋው፤ የአዳማ ከተማ ተጫዋች የሆኑት ሎዛ አበራ፣ሴናፍ ዋኩማ ፣ ሰርካዲስ ጉታ የተካተቱ ሲሆን፤ ምርቃት ፈለቀ ከሀዋሳ ከተማ፣ ሔለን እሸቱ ከመከላከያ እንዲሁም፤ ምስር ኢብራሂም ከጥረት ኮርፖሬት እግር ኳስ ክለብ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። በብሔራዊ ቡድን ጥሪ ከተደረገላቸው 30 ተጫዋቾች መካከል 29 ተጫዋቾች ከአንደኛ ዲቪዝዮን ሲጠሩ የመቐለ 70 እንደርታዋ ዮርዳኖስ ምዑዝ ብቸኛዋ ከሁለተኛ ዲቪዝዮን የተመረጠች ተጫዋች እንደሆኑም ታውቋል። ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ ጨዋታዎች አትሌቲክስን ተጠቅማ ብዙ ታሪክ ብታስ መዘግብም በእግር ኳስ ግን ተሳትፋ አታው ቅም። እ.አ.አ በ2016 በሪዮ ዲጄንየሮ እንዲሁም በ2012 በለንደን በተስተናገደው ውድድር ማጣርያዎች ላይ ያልተሳተፈች ሲሆን በ2008 የቤይጂንግ ኦሎምፒክ እስከ ምድብ ማጣርያ ደርሳ ከደቡብ አፍሪካ ጋር በሜዳዋ አቻ ከተለያየች በኋላ በወቅቱ በፊፋ በተጣለባት እገዳ ምክንያት ከጋና እና ናይጄርያ ጋር ጨዋታ ሳታደርግ ከውድድሩ መውጣቷን መረጃዎች ያመለክታሉ። የእድሜ\nገደብ የሌለው የሴቶች እግር ኳስ ላይ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በሪዮ 2016 ማጣርያ ላይ አልተሳተፈም። በቀደመው (ለንደን 2012) ደግሞ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ 3ለ0 ድምር ውጤት ተሸንፎ ከመጀመርያው ዙር ተሰናብቷል። የማጣርያው አካሄድ ያልታወቀበት ይህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያ ስለመሳተፏ የታ ወቀ ነገር የለም።አዲስ\nዘመን መጋቢት 12/2011ዳንኤል\nዘነበ", "passage_id": "a3c5ab90176b3a940644659dfe9ead9e" }, { "passage": "ግንቦት ወር መጨረሻ ላይ በሩዋንዳ አስተናጋጅነት ለሚደረገው የሴቶች የሴካፋ ዋንጫ ተሳታፊ የሆኑት ሉሲዎቹ በዛሬው እለት ጥሪ ከተደረገላቸው 24 ተጫዋቾች መካከል 23ቱ በተገኙበት የመጀመርያ ልምምዳቸውን ጀምረዋል። በዛሬው ልልምምድ ላይ ያልተገኘችው የድሬዳዋ ከተማዋ ጸጋነሽ ወረቶ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ ከቡድኑ ጋር ተቀላቅላ ልምምድ የማትጀምር ከሆነ አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ በምትኩ ለሌላ ተጫዋች ጥሪ ታቀርባለች ተብሎ ይጠበቃል።ይህ ውድድር በቀጣይ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ከአልጄሪያ ጋር ሰኔ ወር መጨረሻ ላይ ለሚደረገው የመጨረሻ ማጣርያ ወሳኝ ጨዋታ በቂ መዘጋጃ የሚሆን በመሆኑ ተሳታፊ መሆናችን ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግራለች።ግንቦት መጨረሻ  ላይ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የሴቶች የሴካፋ ዋንጫ በሩዋንዳ አስተናጋጅነት የሚካሄድ ሲሆን በቅርቡ የተሳታፊ ሀገራት ብዛት እና የምድብ ድልድሉ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል ።አምና በዩጋንዳ አስተናጋጅነት በተደረገው የሴቶች የሴካፋ ዋንጫ ላይ ሉሲዎቹ በአሰልጣኝ መሰረት ማኒ እየተመሩ ሦስተኛ ደረጃ ይዘው ማጠናቀቃቸው ይታወቃል።", "passage_id": "7d7d8d84305743802a0c3e4c3450bbcf" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ለሚያደርገው የአለም ዋንጫ ቅድመ ማጣርያ በመጪው ማክሰኞ በጋና አድርጎ ወደ ሳኦቶሜ ያቀናል፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ከቦትዋስና ጋር ካደረገው የአቋም መለኪያ ጨዋታ በኋላ ተጫዋቾቹ ያልተበተኑ ሲሆን የዛሬው የአሸናፊዎች አሸናፊ ጨዋታ አድርገው የሚመለሱ ተጫዋቾችን ጨምሮ ከውጭ ሃገር የሚመጡት ዋሊድ አታ እና ሽመልስ በቀለ ወደ ስፍራው ያቀናሉ ተብሏል፡፡ዋሊድ ማክሰኞ አዲስ አበባ ገብቶ ከቡድኑ ጋር ይጓዛል ተብሎ ሲጠበቅ ሁኔታዎች በታቀዱበት ጊዜያት ካልተከናወኑ ለብቻው ወደ ሳኦቶሜ በማቅናት ለጨዋታው ይደርሳል ተብሏል፡፡ የፔትሮጄቱ ኮከብ ሽመልስ በቀለ ማክሰኞ ጠዋት አዲስ አበባ በመግባት ከቡድኑ ጋር አብሮ ይጓዛል ተብሏል፡፡የፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት አቶ ወንድምኩን አላዩ ለሶከር ኢትዮጵያ እንደተናገሩት አምበሉ ሳላዲን ሰኢድ ፣ ጌታነህ ከበደ እና ኡመድ ኡኩሪ ሳኦቶሜን ለመግጠም በሚጓዘው ቡድን ውስጥ አልተካተቱም፡፡ እንደ አቶ ወንድምኩን ገለፃ ሶስቱ ተጫዋቾች የተቀነሱት በአስጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ ውሳኔ ነው፡፡ ሳላዲን ሰኢድ በቅርብ ሳምንታት ለኤምሲ አልጀር በቂ ጨዋታዎችን ማድረግ አልቻለም፡፡ እስካሁን ሙሉ ጨዋታ ያልተሰለፈ ሲሆን የመጨረሻዎቹን 2 ጨዋታዎች ከተጠባባቂ ወንበር ሳይነሳ ጨርሷል፡፡ ጌታነህ ከበደ በውሰት በሚገኝበት ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ፕሪቶርያ የተሸለ የመጫወት እድል ቢያገኝም ግብ ማስቆጠር አልቻለም፡፡ ኡመድ ኡኩሪ ደግሞ በአዲሱ ክለቡ ኢ.ኤን.ፒ.ፒ.አይ ጨዋታ አላደረገም፡፡ የተጫዋቾቹ ወቅታዊ አቋም መልካም አለመሆን አሰልጣኝ ዮሃንስ ይህንን ውሳኔ እንዲወስኑ በር መክፈቱ ቢገመትም አሰልጣኙ ውጪ የሚጫወቱ ተጫዋቾችን በቋሚ አሰላለፋቸው ውስጥ ከማካተት ውጪ አማራጭ እንደሌላቸው በተደጋጋሚ ሲናገሩ መደመጣቸው የሚታወስ ነው፡፡አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ ወደ ቦትስዋና ይዘዋቸው ከሄዷቸው 19 ተጫዋቾች በተጨማሪ በኢትዮጵያ ዋንጫ መልካም አቋም ያሳዩት የመከላከያዎቹ በኃይሉ ግርማ ፣ አዲሱ ተስፋዬ እና ምንይሉ ወንድሙን ወደ ቡድናቸው የቀላቀሉ ሲሆን ዛሬ 6 ተጫዋቾችን በመቀነስና ዋሊድ እና ሽመልስን በማካተት በአጠቃላይ 18 ተጫዋቾችን (አጠቃላይ 26 የልኡካን ቡድን) ማክሰኞ የሳኦቶሜ ጉዟቸውን ይጀምራሉ፡፡የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በመጪው ሀሙስ መስከረም 27 ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር የአለም ዋንጫ የቅድመ ማጣርያ ጨዋታውን የሚያደርግ ሲሆን የመልሱ ጨዋታ ሰኞ ጥቅምት 1 በአዲስ አበባ ስታድየም ይደረጋል፡፡", "passage_id": "737f9ee971373df89b34f119fc2a234d" } ]
a4881e48d8a7a85a6c01e0fbaafc1bc9
a9f22c79ecb8fe111d29a6cf10acf6ce
ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ወጣት ሴት ተማሪዎችን ከስኬታማ ሴቶች ጋር በማጣመር የድጋፍና የምክር አገልግሎት ማስጀመር ውጤታማ ሴቶችን ለማፍራት እንደሚያግዝ ተገለጸ
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡- የመሰናዶ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ወጣት ሴት ተማሪዎች በስራ አለምና በህይወት ተሞክሮ ስኬታማ ከሆኑ ሴቶች ጋር በማጣመር የድጋፍና የምክር አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ፣ ወጣት ሴት ተማሪዎችን ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ አስታወቁ፡፡የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ሴት ተማሪዎች ውጤታማ ሆነው እንዲወጡ ከስኬታማ ሴቶች ጋር የምክክርና ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ እንደተናገሩት፤ 12ኛ ክፍልን በጥሩ ሁኔታ አጠናቀው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ሴቶችን የደጋፊና መካሪ አገልግሎት እንዲያገኙ በህይወታቸው ስኬታማ ሴቶች ጋር ጥምረት እንዲፈጠር መደረጉ መንግስት ሴቶችን ወደ አመራር ለማምጣት ለሚያደርገው ጥረት አጋዥ ነው፡፡ በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚውና በማህበራዊው ዘርፍ ስኬታማ የሆኑ ሴቶች፣ ለወጣት ሴት ተማሪዎች የድጋፍና የምክር አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ትልቅ ስኬት ነው፡፡ እንደ ፕሬዚዳንቷ ገለፃ፤ ወጣት ሴት ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሲቀላቀሉ የሚሄዱት አዲስ አካባቢና አዲስ ሁኔታ ውስጥ እንደመሆኑ ብዙ ውጣውረዶች ይገጥሟቸዋል፡፡ በዚህ ወቅት የሚደግፋቸውና የሚመክራቸው መኖሩ በራስ የመተማመን አቅማቸውን አሳድገው አንገታቸውን ቀና ሊያደርግ፤ የአስተሳሰብ አድማሳቸውን በማስፋት የሚጎሏቸው ነገር ላይ በመምከር የበለጠ ሊያዘጋጇቸው የሚችል ነው፡፡ የደጋፊና መካሪ ስራ ደግሞ በቃላት ብቻ ሊገለፅ የማይችል ጥቅም ስላለው ለተማሪዎች በትምህርታቸው ላይም ሆነ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደስራ ዓለም ለመቀላቀል በሚዘጋጁበት ጊዜም ትልቅ አቅም ይፈጥርላቸዋል፡፡ በተለይም እንደተምሳሌት የሚያዩአቸው ሴቶች መኖራቸው ወደፊትም ለሚኖራቸው ራዕይ አርቀው እንዲያስቡ ያግዛቸዋል፡፡ ምክንያቱም የወጣት ሴት ተማሪዎች የደጋፊና የመካሪ መርሃ ግብር መጀመሩ በተለይም የወደፊት ራዕያቸውን በመመልከት በሚገጥማቸው ፈተና ሳይደናገጡ አላማቸውን ለማሳካት ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ከዚህ በፊት ያለፍንበት ሁኔታ እንድንፎካከር እንጂ እንድንደጋገፍ የሚረዳ አልነበረም ያሉት ፕሬዚዳንቷ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ምንም አይነት ችግር ሳይበግራቸው ለስኬት የበቁ ሴቶችን አብነት በመውሰድ ወጣት ሴት ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ለትልቅ ኃላፊነት ራሳቸውን ሊያዘጋጁ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ በዚህ ረገድ የደጋፊና የመካሪ አገልግሎት መርሃ ግብር መጀመሩ መልካም እድል መሆኑን በመጥቀስ፤ አንድ ስኬታማ ሴት የደገፈቻትና ያማከረቻት ተማሪ ለኃላፊነት በቅታ ማየቷ የራሷ ስኬት አድርጋ ልትቆጥረው እንደሚገባ፤ ይህ ሲሆን የምክርና ድጋፍ አገልግሎት መስጠት በሁለቱም ወገን ጥቅም ከፍተኛ እርካታ እንዳለው ተናግረዋል፡፡አገልግሎቱ ከ45 ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ 50 ለሚሆኑ ተማሪዎች ሲሆን፤ ከአንድ ወር በኋላ ከአንድ ሺ 500 በላይ የሁለተኛና ከዚያ በላይ ያሉ ተማሪዎች የምክርና ድጋፍ አገልግሎት እንደሚጀምር ተነግሯል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37853
[ { "passage": "የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ከሚል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ሚኒስቴሩ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ላለፉት አመታት ጥናትን መሰረት ባደረገ መልኩ በሁለት አበይት ጉዳዮች ላይ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።የብሄራዊ ህብረተሰብ ተኮር ምክክር እና ወጣቶችን ያማከለ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ጥናት አድርገን እየሰራን እንገኛለን ያሉት ሚኒስትሯ፣ የምክክር መድረኩ በማህበረሰብ እንዲሁም በሊህቃን ደረጃ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።ውይይቱ ከቀበሌ እና ጎጥ ጀምሮ ማህበረሰቡን በማካተት የሚካሄድ ሲሆን፣ በልሂቃኑ ዘርፍ ደግሞ የፓለቲካ ፓርቲዋች፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ ፓለቲከኞች፣ የታሪክ ምሁራን እና ሌሎች በየዘርፋ እየተሳተፉበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።ዘላቂ ሰላምን ለመፍጠር የወጣቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የገለጹት ወ/ሮ ሙፈሪሃት፣ ባሳለፍነው አመት ብቻ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋም ተመርቀው የተመዘገቡ 116ሺህ ወጣቶች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡በአስር ዮኒቨርስቲዋች ውስጥ የመጀመሪያው ዙር ስልጠና 35ሺህ ወጣቶችን በሶስት ዙር ለማሰልጠን እንቅስቃሴ መጀመሩንም አንስተዋል።ለ45 ቀናት በሚቆየው በዚህ ስልጠና ወጣቶች በስነ ልቦና ውቅር፣ በስሜት ብስለት እንዲሁም በስራ የመፍጠር ባህል እንዲያዳብሩ የሚያግዝ ነው ተብሏል።ወጣቶቹ ስልጠናቸውን ሲጨርሱ ለ10 ወራት በአገሪቱ የተለያዩ አቅጣጫዎች ተሰማርተው ልምድ በመቅሰም አዲስ ባህል እና ልምድን ያገኛሉ የተባለ ሲሆን፣ በተማሩበት የትምህርት ዘርፍ ወርደው ማህበረሰቡን እንደሚያገልግሉም ተገልጿል።(በቁምነገር አህመድ)", "passage_id": "33900659df884dde5fdf7a6dedbfd25d" }, { "passage": "ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!የትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ነቢል መህዲ በአሁኑ ጊዜ የሴት ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ እንደ ሀገር ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ሴት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ከማምጣት ባሻገር በትምህርት ገበታቸው እንዲቆዩና ለውጤት እንዲበቁ አሁንም ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑን እና የትምህርት ተቋማት ለሴት ተማሪዎች ምቹና ከትንኮሳ የፀዱ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ወሲባዊ፣ አካላዊና ስነ ልቦናዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጥቃቶችን ለመቅረፍ ሁሉም ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣት ይገባዋል መባሉን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ ", "passage_id": "364fa447f7aabdaccb6e0f9c7cc43264" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ የካቲት 27 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ብቁ የሰው ኃይል በማፍራትና ምርምር ከማከናወን ባለፈ የዲፕሎማሲ ኃይል መሆን እንደሚጠበቅባቸው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ገለፁ።“የዩኒቨርሲቲ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አንድ እርምጃ ወደፊት ለማራመድ ጠንካራ አመራር”በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ “የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ብቁ የሰው ኃይል በማፍራት ችግር ፈቺና የኢንዱስትሪ ምርታማነትን የሚያሳድግ እንዲሁም ግብርናን የሚያዘምን ምርምር ከማከናወን ባሻገር የዲፕሎማሲ ኃይል መሆን ይጠበቅባቸዋል” ብለዋል።በዩኒቨርሲቲ እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንዱስትሪ ትስስር ፎረሙ ዩኒቨርሲቲዎች በሚሳተፉባቸው አህጉራዊና ዓለም አቀፍ መድረኮች ኢትዮጵያ የምትከተለውን የብሔራዊ ጥቅም አተያይ ለማስገንዘብ መስራት እንደሚኖርባቸውም ተገልጿል።የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ብሄራዊ ጥቅምን መነሻ የሚያደርግ በትብብርና በፉክክር ሚዛን አስጠብቆ የሚከናወን እንደሆነም ጠቁመዋል።በተጨማሪ “ዩኒቨርሲቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም በላቀ ደረጃ የሚረጋገጥበትን ሥልት በጥናት ለይቶ ከማመላከት አልፈው በሚሳተፉባቸው አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረኮች ላይ የብሔራዊ ጥቅም አተያይን ማስገንዘብ ይኖርባቸዋልም” ነው ያሉት።ከታላቁ የህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘም በድርድር በሚመጣ መፍትሔ ውስጥ የሃገርን ጥቅም የሚያስጠብቅ ውጤት እንዲገኝ የትምህርት ተቋማት ብዙ መስራት እንዳለባቸው አመላክተዋል።በዛሬው እለት የተጀመረው የምክክር መድረክ ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!\nhttps://t.me/fanatelevision", "passage_id": "04b0f9b600f39e057aa1d74757c0f579" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ተመራቂዎች ያገኙትን ዕውቀት በሥራ ላይ በማዋል ለራሳቸው፣ ለቤተሰቦቻቸው እና ለአገራቸው ጠቃሚ እንዲሆኑና የአገር ልማትን በማጠናከር ረገድም አርአያ መሆን እንደሚገባቸው የዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ አስገነዘበ፡፡ ዩኒቨርሲቲው\nበቡራዩ\nገፈርሳ\nካምፓስ\nበልዩ\nልዩ\nየትምህርት\nዓይነት\nያሠለጠናቸውን\nተማሪዎች\nትናንት\nባስመረቀበት\nወቅት\nየዩኒቨርሲቲው\nምክትል\nፕሬዚዳንት\nዶክተር\nተስፋዬ\nተሾመ\nእንደተናገሩት፣\nተመራቂዎች ያገኙትን ዕውቀት በሥራ ላይ በማዋል የአገር ልማትን በማጠናከር ረገድ አርአያ እንዲሆኑ አደራ ብለዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት አክለው እንዳሉት ለማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የመማር ማስተማር፣ ጥናትና ምርምር ማካሄድ እና የኅብረተሰብ አገልግሎት መስጠት ዩኒቨርሲቲ የሚያ ስብሉት ዓቢይ ተግባራት ናቸው፡፡ ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲም እንደ አንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የመማር ማስተማር ሂደቱን በጥራት ለማከናወን ላለፉት ዓመታት የሚቻለውን ትኩረት በመስጠት እየተንቀሳቀሰ መቆየቱን ገልጸው ዩኒቨርሲቲው የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራትና የጥራቱም ሂደት ቀጣይ እና አስተማማኝ እንዲሆን ሳያሰልስ እንደሚሠራ አብራርተዋል፡፡ የቡራዩ ገፈርሳ ካምፓስ ዲን\nዶክተር\nሙሉጌታ\nታየ\nበበኩላቸው\nየእንኳን\nደህና\nመጣችሁ\nመልዕክታቸውን\nካስተላለፉ\nበኋላ\nየመጀመሪያ\nዙር\nተመራቂ\nተማሪዎች\nየዕድሜ\nዘመን\nየቡራዩ\nገፈርሳ\nካምፓስ\nአምባሳደር\nእንደሆኑ\nተናግረዋል፡፡\nበካምፓሱ የሚማሩ የተማሪዎች ቁጥርንም ለማሳደግ በማሰብ ከዩኒቨርሲው ጋር\nተመጋጋቢ\nየሆነ\nከኬጂ\nእስከ\nዩኒቨርሲቲ\nየሚለውን\nየትምህርት\nስልት\nተግባራዊ\nለማድረግ\nመሠረት\nእየተጣለ\nእንደሆነ\nገልጸዋል፡፡\n«ካምፓሱን ለማሳደግ የተለያዩ የማስ ፋፊያ እና\nየማጠናከሪያ\nሥራ\nመስራት\nአለብን»\nያሉት\nዶክተር\nሙሉጌታ\nይህ\nንንም\nለመተግበር\nየአካባቢውን\nሕዝብ\nበማስ\nተባበርና\nከሚመ\nለከታቸው\nቢሮዎች\nጋር\nበመሆን\nእንደሚሰሩም\nጠቁመዋል፡፡\nከነፃ የትምህርት ዕድል ጋር በተያያዘ የአካባቢውን ሕዝብ ለማበረታታት በዩኒቨ ርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አረጋ ይርዳው ለአምስት ተማሪዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት እንዲማሩ የነፃ ዕድል እንደተሰጠም በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 30/2011", "passage_id": "2085174986c82ae0ce37ec663af8e646" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥር 3 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ )የብሔራዊ የበጎ ፈቃድ የማህበረሰብ አገልግሎት ትኩረት ብቁ ወጣት በማፍራት ዘላቂ ሰላሟ የተረጋገጠ ሀገር መገንባት መሆኑን የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።", "passage_id": "53735d00f5d1626a5bb3d20d5b855f7e" } ]
76acdd720cf636a1cd3bf484b22bc72b
fc20029fb20961311b63db235f127f99
ዋልያዎቹ በሴካፋ ዋንጫ ከዩጋንዳ ጋር ተደልድለዋል
የ2019 የመካከለኛውና ምስራቅ አፍሪካ ዋንጫ(ሴካፋ) በዩጋንዳ አዘጋጅነት ከህዳር 27 እስከ ታህሳስ 9 ይካሄዳል፡፡ ውድድሩ በሦስት ምድብ ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ በምድብ አንድ ከኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ጋር ተደልድለዋል፡፡ በዚሁ ምድብ አዘጋጇ ዩጋንዳና ቡሩንዲም ተደልድለዋል፡፡ በምድብ ሁለት በተጋባዥነት የምትሳተፈው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከሱዳን፣ ደቡብ ሱዳንና ሶማሊያ ጋር የተደለደለች ሲሆን በመጨረሻው ምድብ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ጅቡቲና ዛንዚባር መደልደላቸው ታውቋል፡፡ ርዋንዳ በዚህ ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ ትሆናለች ተብሎ ቢጠበቅም በበጀት እጥረት እንደማትካፈል ተረጋግጧል፡፡ ርዋንዳ በዚሁ የውድድር ዓመት በዩጋንዳ አዘጋጅነት ተካሂዶ በነበረው ከአስራ ሰባት ዓመት በታች የሴካፋ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ ምክኒያት ካለመሳተፏ ባሻገር ከቀናት በፊት በታንዛኒያ አዘጋጅነት ተካሂዶ በተጠናቀቀው የሴቶች ሴካፋ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ ምክኒያት መሳተፍ አለመቻሏ ይታወሳል ዋልያዎቹ ከሳምንት በፊት ለ2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድባቸውን ሁለተኛ ጨዋታ ባህርዳር ላይ በማድረግ ትልቅ የእግር ኳስ ደረጃ ያላትን ኮትዲቯርን ሁለት ለአንድ በሆነ ውጤት ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡ ይህም በቡድኑ ላይ ትልቅ መነቃቃት የፈጠረ ቢሆንም ቀጣዩን የማጣሪያ ጨዋታ ከበርካታ ወራት በኋላ ለሚያደርጉት ዋልያዎቹ ስጋት እንዳለው ሲነገር ቆይቷል፡፡ ዋልያዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያውን ነሐሴ ወር ላይ ማካሄዳቸው አሁን የተፈጠረውን መነቃቃት እንዳያደበዝዘው እንደ ሴካፋ አይነት ውድድሮች አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ ዋልያዎቹ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ የወዳጅነት ጨዋታዎችን በብዛት ማድረግ አለመቻላቸው ካተቀረፈ፣ የቡድኑ ስብስብም ለረጅም ጊዜ ተለያይቶ ሲገናኝ አሁን ያለው የአሸናፊነት መንፈስና መነቃቃት በነበረበት ላይገኝ ይችላል የሚሉ ስጋቶች አሉ፡፡ ዋልያዎቹ ቀጣዩን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ እስኪያደርጉ ቻንን በመሳሰሉ ዋንጫዎች አለመሳተፋቸው ተጨማሪ ጉዳት ቢሆንም እንደ ሴካፋ አይነት ውድድሮች ላይ መሳተፍ መቻላቸው አሰልጣኝ አብረሃም መብራቱ ቡድኑን ለመገንባት በሚያደርጉት ሂደት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 17/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23237
[ { "passage": "\nበአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ (ቻን) ሁለተኛ ዙር ማጣርያ ኢትዮጵያን የምትገጥመው ሩዋንዳ ለጨዋታው ወደ መቐለ ከማምራቷ በፊት የአቋም መለኪያ ታደርጋለች።ከአራት ቀናት በፊት ለ26 ተጫዋቾች ጥሪ አድርገው በአሰልጣኝ ቪሰንት ማሻሚ እየተመሩ ዝግጅት የጀመሩት ሩዋንዳዎች ከሁለት ቀናት በኋላ በቻን ውድድሮች ጥንካሬዋን ያሳየችው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ይገጥማሉ። በስታደ ኪጋሊ ልምምድ በማድረግ ላይ የሚገኙት ‘አማቩቢ’ዎቹ ከወዳጅነት ጨዋታው ቀጥሎ ባለው ቀን አዲስ አበባ ገብተው በዛው ቀን ጨዋታው ወደሚደረግበት መቐለ እንደሚያመሩ ለማወቅ ተችሏል።ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች በቻን ውድድር ማጣርያ ለሦስተኛ ጊዜ የሚገናኙ ሲሆን የመጀመርያውን (2014) ኢትዮጵያ፤ ቀጣዩን (2018) ደግሞ ሩዋንዳ አሸንፈው ለውድድሩ ማለፋቸው ይታወሳል። በተለይም በ2018ቱ ማጣርያ ሩዋንዳ አዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ኤሩክ ሩታንጋ፣ ሙሐጅር ሐኪዝማና እና ዓብዲ ቢራማሂሬ ባስቆጠሯቸው ጎሎች 3-2 አሸንፋ መመለሷ ይታወሳል።", "passage_id": "2b76c15ea2ac7e2ac451bf6d85abfa72" }, { "passage": "በኬንያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የሴካፋ ሲኒየር ቻሌንጅ ካፕ ኢትዮጵያ ማክሰኞ በ9፡00 ደቡብ ሱዳንን በመግጠም የምድብ ጨዋታዋን ትጀምራለች።የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛሬ ከ4:55 ጀምሮ በካካሜጋ ትምህርት ቤት ሜዳ ልምምዱን ሰርቷል። ዋሊያዎቹ በካካሜጋ ከተማ ሲያ ገስት ሃውስ ከሐሙስ ጀምሮ መቀመጫውን አድርጎ ለሴካፋ ሲኒየር ቻሌንጅ ዋንጫ የምድብ ሁለት ጨዋታ ዝግጅቱን ቀጥሏል።ብሄራዊ ቡድኑ ቀለል ያለ ልምምድ ዛሬ ያከናወነ ሲሆን ከተስፋዬ አለባቸው በቀር 22ቱም ተጨዋቾች በልምምዱ ላይ ሲሳተፉ ከጉዳት እያገገመ የሚገኘው አማካዩ ተስፋዬ ለብቻው ቀላል ያሉ እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ ተስተውሏል። ነገ ከደቡብ ሱዳን ጋር ላለው ጨዋታም የመድረሱ ነገር አጠራጣሪ ነው። ቢሆንም ለቀጣዮቹ ጨዋታዎች ግን እንደሚደርስ ይጠበቃል።ማክሰኞ ህዳር 268፡00 – ዛንዚባር ከ ሩዋንዳ (ማቻኮስ)9፡00 – ኢትዮጵያ ከ ደቡብ ሱዳን (ካካሜጋ)10፡00 – ኬንያ ከ ሊቢያ (ማቻኮስ)ሐሙስ ህዳር 288፡00 – ታንዛኒያ ከ ዛንዚባር (ማቻኮስ)9፡00 – ኢትዮጵያ ከ ብሩንዲ (ካካሜጋ)10፡00 – ሩዋንዳ ከ ሊቢያ (ማቻኮስ)አርብ ህዳር 299፡00 – ዩጋንዳ ከ ደቡብ ሱዳን (ካካሜጋ)ቅዳሜ ህዳር 308፡00 – ሩዋንዳ ከ ታንዛኒያ (ማቻኮስ)10፡00 – ኬንያ ከ ዛንዚባር (ማቻኮስ)እሁድ ታህሳስ 19፡00 – ኢትዮጵያ ከ ዩጋንዳ (ካካሜጋ)ሰኞ ታህሳስ 28፡00 – ሊቢያ ከ ዛንዚባር (ማቻኮስ)9፡00 – ደቡብ ሱዳን ከ ቡሩንዲ (ካካሜጋ)10፡00 – ኬንያ ከ ታንዛኒያ (ማቻኮስ)የሴካፋ ሲኒየር ቻሌንጅ ዋንጫ በሶከር ኢትዮጵያ እንዲቀርብ ያስቻለው ጎ ቴዲ ስፖርት ነው፡፡ ጎ ቴዲ ስፖርት በኢትዮጵያ የማራቶን ትጥቆች ወኪል አከፋፋይ!!", "passage_id": "bd93c512ad84e0ed42dbe69a00a71bae" }, { "passage": "በቻን ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያን የምትገጥመው ሩዋንዳ በቀጣዩ ሰኞ ታንዛኒያን በወዳጅነት ጨዋታ በሜዳዋ ታስተናግዳለች፡፡በአሰልጣኝ ማሻሚ ቪንሰንት የሚመሩት ሩዋንዳዎች ከቀናት በፊት በመቀለ ዓለምአቀፍ ስታዲየም ኢትዮጵያን 1ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወደ 2020 የቻን አፍሪካ ዋንጫ የተሻለ የማለፍ እድልን ይዘው ለመልስ ጨዋታ የተሻለ እድልን ሰንቀው መመለሳቸው ይታወሳል። በቀጣይ ላለባቸው የመልስ ጨዋታ እንዲሁም በቅርቡ ለሚጀመረው የ2021 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅት ይረዳቸው ዘንድም ሌላኛዋ የምስራቅ አፍሪካ ሀገር ታንዛኒያን በቀጣዩ ሰኞ በኪጋሊ ስታዲየም የሚገጥሙ ይሆናል፡፡ሩዋንዳዎች ከኢትዮጵያ ጋር ካደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ በፊት በወዳጅነት ጨዋታ ዲሪ. ኮንጎን 3-2 ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡ሩዋንዳ ኢትዮጵያን አሸንፋ ለ6ኛው የአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ ከበቃች በታሪኳ ለአራተኛ ጊዜ የምትሳተፍ ይሆናል፡፡", "passage_id": "491cfb9e36cb9267590666f488f6b771" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በወዳጅነት ጨዋታ ከዛምቢያ እና ታንዛኒያ ጋር እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡ ዋሊያዎቹ ጋቦን ለምታዘጋጀው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ማጣሪያው ሰኔ 7 ከሌሴቶ ጋር ለሚደርገው ጨዋታ የሚጠቅሙ የተባሉ ሁለት የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች የሚያደርግ ይሆናል፡፡ ዋሊያዎቹ ከ2012 የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ዛምቢያ ጋር ከሰኔ 1-4 ባሉት ቀናት የሚጫወቱ ይሆናል፡፡ የታንዛኒያ ብሄራዊ ቡድን ከግንቦት 27 ጀምሮ አዲስ አበባ ላይ ልምምድ ይሰራል፡፡ ታይፋ ስታርስ በሚል ስም የሚታወቁት ታንዛኒያዎች ከግብፅ ጋር ላለባቸው አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ጨዋታ ከኢትዮጵያ ጋር የአቋም መለኪያ ጨዋታ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ተነግሯል፡፡ ታንዛኒያ እና ዛምቢያ አሁን እየተደረገ ባለው የኮሳፋ ዋንጫ ላይ ተሳትፎ አድርገዋል፡፡ በቀድሞ የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰልጣኝ ማርት ኖይ የሚሰለጥነው የታንዛኒያ ብሄራዊ ቡድን በኮሳፋ ዋንጫ ከምድቡ ማለፍ አልቻለም፡፡ በሆነር ጃንዛ የሚመሩት ቺፖሎፖሎዎቹ በሩብ ፍፃሜ በናሚቢያ ተሸንፈው ከውድድሩ ውጪ ሆነዋል፡፡ ኢትዮጵያ ምድብ ውስጥ ያሉት ሲሸልስ እና ሌሴቶ በኮሳፋ ዋንጫ ከምድባቸው ማለፍ አልቻሉም፡፡ ሁለቱ የወዳጅነት ጨዋታዎች ኢትዮጵያን እንደሚጠቅሙ ታምኖበታል፡፡የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ጁነዲ ባሻ ዛሬ በግል የትዊተር ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ ፌድሬሽኑ የወዳጅነት ጨዋታ ለዋሊያዎቹ ለማዘጋጀት እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡‹‹ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለብሔራዊ ቡድኑ የቻን 2016 እና የአፍሪካ ዋንጫ 2017 የማጣሪያ ጨዋታዎች ዝግጅት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ተዘጋጅቷል:: የወዳጅነት ጨዋታዎችን ለማድረግም ከስምምነት ደርሰናል:: ›› ", "passage_id": "3b88ad25b102dbe8156028f88c5bd28d" }, { "passage": "ጋቦን ለምታስተናግደው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሚደረጉ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዎች በነሃሴ ወር መጨረሻ ይገባደዳሉ፡፡ለአፍሪካ ዋንጫው የማለፍ እጅግ በጣም የጠበበ ዕድል ያላት ኢትዮጵያ ሲሸልስን ሃዋሳ ላይ ታስተናግዳለች፡፡ ጨዋታው አርብ ነሃሴ 27 በ10:00 እንዲካሄድ ካፍ የወሰነ ሲሆን የጨዋታ ዳኞቹ ከዩጋንዳ እንደሆኑ ታውቋል፡፡የምድብ 10 የመጨረሻ ጨዋታ የሚመሩት ዋና ዳኛ ብራያን ሚሮ ናሱቡጋ፣ ረዳቶቹ ማርክ ሶንኮ እና ሁሴን ቡጌምቤ ናቸው፡፡ ብሪያን ናሱባጋ በ2015 ዩጋንዳ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታን በአራተኛ ዳኝነት እየመራ ጨዋታው የተቋረጠ ሲሆን የዩጋንዳ እግርኳስ ማህበር (ፉፋ) ካገዳቸው ዳኞች መካከል ነበር፡፡ እግዱ ወዲያው የተነሳለት ብሪያን ከዚህ ቀደም በ2013 የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን ቱኒዚያን አዲስ አበባ ላይ 3-0 በ2013 ሲያሸንፍ ጨዋታውን በመሃል ዳኝነት መምራት ችሏል፡፡ዋሊያዎቹ በሃዋሳ ከትመው ዝግጅታቸውን እያደረጉ ሲሆን የምድብ አምስተኛው መርሃ ግብር ጨዋታቸውን ሌሶቶን በጌታነህ ከበደ ሁለት ግቦች 2-1 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ከምድብ አስር አልጄሪያ አስቀድማ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈች በመሆኑ ኢትዮጵያ ጥሩ ሁለተኛ ሆኖ የማለፍ ተስፋዋ በሌሎች የምድብ ጨዋታች ውጤቶች ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ", "passage_id": "ff83f567283a227d180835c50169892b" } ]
1c82a9513a6040325d887cac1122f0e1
d94b6faf5448369e27cea8d63ea2e5df
ኢትዮጵያውያን የደመቁባቸው ዓለም አቀፍ ክብሮች
 የዓመቱ የምርጥ አትሌቶች ሽልማት እጩዎች ከሦስት ሳምንት በፊት ይፋ ሲደረግ አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት ከምርጥ አስር እጩዎች ውስጥ መካተት አልቻለም ነበር። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይህን ክብር ደጋግመው ማግኘት ቢችሉም ባለፉት ሁለት ዓመታት በሁለቱም ፆታ ከእጩዎቹ መካከል እንኳን ሳይካተቱ መቅረታቸው አስገራሚ ነበር። ያም ሆኖ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዋናው ሽልማት በእጩነት ያልተካተቱበት አጋጣሚ በወጣቶች ወይም ከሃያ ዓመት በታች በእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ አትሌቶች በሚሳተፉበት ሽልማት ሁለት ወንዶችና አንድ ሴት አትሌት መካተት ችላለች። ከእጩነት ባሻገርም ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ሽልማቱን ማሸነፍ ችሏል። ባለፈው ቅዳሜ በሞናኮ በተካሄደው የሽልማት ስነስርዓት ላይ ኢትዮጵያውያን በኮማንደር ደራርቱ ቱሉ አማካኝነት ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ሽልማት ማግኘት ችለዋል። እኤአ 1992ና 2000 ላይ በተካሄዱት የባርሴሎናና የሲድኒ ኦሊምፒኮች በአስር ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎችን ያጠለቀችው ጀግናዋ አትሌት ደራርቱ ቱሉ በዓለም አትሌቲክስ ‹‹ዘንድ የዓመቱ ምርጥ ሴት›› በሚል ሽልማት አግኝታለች። ደራርቱ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንትነት እየመራች ላሳየችው የላቀ አስተዋፅኦ ይህ እውቅና ተችሯታል። ደራርቱ በአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን የምክር ቤት አባል ስትሆን የምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆንም እያገለገለች መገኘቷ ለሽልማቱ አብቅቷታል። የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ኢትዮጵያዊ አትሌት ሰለሞን ባረጋ የዘንድሮውን ዓመት የወጣትና ተስፈኛ አትሌቶች ሽልማት ለመጀመሪያ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል። ሰለሞን በዶሃ በተካሄደው የዓለም ቻምፒዮና በአምስት ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ከማጥለቁ በተጨማሪ በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና አምስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። በውድድር ዓመቱ የዓለም ከሃያ ዓመት በታች የአምስትና አስር ሺ ሜትር ርቀቶችን 12፡53፡04ና 26፡49፡46 በሆነ ጊዜ መሪ ሰዓቶች ማስመዝገቡ ለሽልማቱ አብቅቶታል። ባለፉት ሁለት ዓመታት በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች ድንቅ ብቃት እያሳየ የሚገኘው አትሌት ሰለሞን ባረጋ ባለፈው ዓመትም ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ስም ዝርዝር ውስጥ መካተቱ ይታወሳል።የደቡብ ፖሊሱ ክለብ አትሌት የሆነው ሰለሞን ባረጋ ከእድሜው ከፍ ብሎ ከታላላቆቹ ጋር በመወዳደር እያስመዘገበ ላለው ስኬት ባለፈው ዓመት ክለቡ የኢንስፔክተርነት ማዕረግ የሰጠው ሲሆን ባለፉት ሦስት ዓመታት እያሳየ ያለው አስደናቂ ብቃት ወደ ፊት ተስፋ እንዲጣልበት አድርጓል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ወደ ታላላቅ የውድድር መድረኮች መጥቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስፖርት ቤተሰቡ አይን ማረፊያ የሆነው ወጣት አትሌት ሰለሞን ባረጋ ውጤቱና አስደናቂ ብቃቱ ኢትዮጵያ በቅርቡ በታላላቅ መድረኮች አረንጓዴውን ጎርፍ ዳግም የማየት ብሩህ ተስፋ እንዳላት ማሳያ መሆኑን በርካቶች ይመሰክሩለታል። ድንቅ የሩጫ ተሰጥኦው በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች በቅርብ ጊዜ ውስጥ ዙፋን ላይ እንደሚወጣ የስፖርቱ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ መስክረውለታል። በ2018 የውድድር ዓመት የአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊ መሆን የቻለው ሰለሞን ባረጋ በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች የዓለም ክብረወሰንን 12፡ 43፡02 በሆነ ሰዓት ከመጨበጡ ባሻገር እኤአ 2005 ላይ ቀነኒሳ በቀለ በርቀቱ ካስመዘገበው ሰዓት ወዲህ ፈጣን ሰዓት ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሦስት ሺ ሜትር መሰናክል የብር ሜዳሊያ እንድታገኝ ያስቻለው አትሌት ለሜቻ ግርማ ከአምስቱ ተስፈኛ እጩዎች መካከል አንዱ በመሆን ከሰለሞን ጋር ሽልማቱን ለማሸነፍ ተፎካክሯል። ለሜቻ በውድድር ዓመቱ በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች መሪ የሆነውን ሰዓት በ8፡01፡36 ያስመዘገበ ሲሆን የኢትዮጵያን ክብረወሰንም የግሉ ማድረግ ችሏል። በዓለም ቻምፒዮናውም የወርቅ ሜዳሊያ ያመለጠው በ0ነጥብ01 ማይክሮ ሰከንድ ተቀድሞ እንደነበረ አይዘነጋም። ከሁለቱ ኢትዮጵያን እጩዎች ጎን ለጎን ብራዚላዊው የአራት መቶ ሜትር መሰናክል ተወዳዳሪ አሊሰን ዶስ ሳንቶስ፣ ኖርዌያዊው አትሌት ጃኮብ ኢንግብሪትሰን፣ ዩክሬናዊው መዶሻ ወርዋሪ ማይክሃይሎ ኮክሃን በሽልማቱ ተፎካካሪ ነበሩ። በወጣት ሴቶች ዘርፍ ከሰለሞን ባረጋ ጋር ተመሳሳይ ሽልማት ማሸነፍ የቻለችው ዩክሬናዊታ ያሮስላቫ ማሁቺክ ናት። ይህች አትሌት በከፍታ ዝላይ የተሻለ አቅም ያላት አትሌት ስትሆን 2 ሜትር ከ04 ሳንቲ ሜትር በመዝለል የክብረ ወሰን ባለቤት ናት። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮናም የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። ከዚህም ባሻገር አውሮፓ ቻምፒን መሆን የቻለች ጠንካራ አትሌትም ናት። ይህን ሽልማት ለማሸነፍ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለምለም ኃይሉ ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ውስጥ ተካታ ተፎካካሪ መሆን ችላለች። ጃማይካዊቷ ብሪታኒ አንደርሰን፣ የኢኳዶሯ እርምጃ ተወዳዳሪ ግሌንዳ ሞርጆን፣ አሜሪካዊቷ 100 ሜትር የወጣቶች ባለክብረወሰን ሻካሪ ሪቻርድሰን የመጨረሻዎቹ ተፎካካሪዎች ነበሩ። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከእጩዎች መካከል ያልተካተቱበት የዓመቱ የምርጥ አትሌቶች ሽልማት በወንዶች ዘርፍ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል። የማራቶን ፈርጡ ኢሉድ ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ ሁለት ፉክክሮች ላይ ብቻ ቢታይም ያስመዘገበው ታሪክ ሽልማቱን ለማሸነፍ አብቅቶታል። ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ የለንደን ማራቶንን ክብረወሰን በማሻሻል በ2፡02፡37 ሰዓት ማሸነፉ ይታወሳል። ከዚህ በላይ ግን ከወር በፊት በቬና ማራቶን የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ያሳየበት ውድድር አይዘነጋም። ኪፕቾጌ ከትጥቅ አምራች ኩባንያው ናይኪ ጋር በመሆን በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ታግዞም ቢሆን ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች ማጠናቀቅ እንደሚቻል አስመስክሯል። 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማራቶንን በማጠናቀቅ በታሪክ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆን ቢበቃም የተመዘገበው ሰዓት በዓለም ክብረወሰንነት እንዳልተያዘ ይታወሳል።ያም ሆኖ ዓለም ዓቀፍ ሽልማቱን ከማሸነፍ አላገደውም። ባለፈው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአስር ሺ ሜትር ቻምፒዮን የሆነው ዩጋንዳዊው ጆሹአ ቺፕቴጌ የመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች መቀላቀል የቻለ ሲሆን፣ አሜሪካዊው ምርኩዝ ዘላይ ሳም ኬንድሪክስ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው አስራ ሰባት ከቤት ውጪ ውድድሮች አስራ ሁለቱን በድል በማጠናቀቅ የሽልማቱ ተፎካካሪ ነበር።አሜሪካዊው የአጭር ርቀት አትሌት ኖህ ላይልስና ኖርዌያዊው የአጭር ርቀት ኮከብ አትሌት ካርልስተን ዋርሆልም የሽልማቱ ተፎካካሪ ነበሩ። በሴቶች መካከል የተደረገውን ሽልማት አሜሪካዊቷ ደሊላ ሙሃመድ አሸንፋዋለች። በዓመቱ በ400 ሜትር ያሳየችው አቋም ለሽልማቱ ያበቃት ሲሆን አትሌቷ በሃገር አቀፍ ቻምፒዮና 52ሰከንድ ከ20ማይክሮ ሰከንድ መበመግባት ቀዳሚ ናት። በ400 ሜትር መሰናክል በራሷ የተያዘውን ክብረወሰን 52ሰከንድ ከ16ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ብቃቷን አስመስክራለች። በ4በ 400 ሜትርም በተመሳሳይ የዓለም ቻምፒዮን ናት። በርዝመት ዝላይ ቬንዙዌላዊቷ ዩሊማር ሮጃስ ለመጨረሻው ዙር በመድረስ የተፎካከረች ሲሆን የአጭር ርቀት ተወዳዳሪዋ ጃማይካዊት አትሌት ሼሊ- አን ፍራዘር-ፕረይሲ፣የማራቶን ክብረወሰንን ሰበረችው ኬንያዊት አትሌት ብርጊድ ኮስጊ፣በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በ1ሺ500 እና10ሺ ሜትር አሸናፊ የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትልት ሲፋን ሃሰን ለመጨረሻ እጩነት ቀርበው ተፎካካሪ ሆነዋል።አዲስ ዘመን  ህዳር 16 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23174
[ { "passage": "በ25 ዓመታት የውድድር ዘመኑ፤ በርካታ የኦሊምፒክና የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ሜዳሊያዎችን እንዲሁም 27 የዓለም ክብረወሰኖችን በእጁ አስገብቷል። በረጅም ርቀት የመም ተወዳዳሪዎችም ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፤ ከገጹ ፈገግታ የማይነጥፈው ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ። በስድስት ዓለም ቻምፒዮናዎች ተሳትፎው አራት የወርቅ፣ ሁለት የብርና አንድ የነሃስ በጥቅሉ ሰባት ሜዳሊያዎችን ለሃገሩ አበርክቷል። እአአ 1993 የስቱትጋርት ቻምፒዮና የመጀመሪያ ተሳትፎው ሲሆን፤ በ10ሺ ሜትር የወርቅ በ5ሺ ሜትር ደግሞ የብር ሜዳሊያ ነበር ያጠለቀው። ከሁለት ዓመታት በኋላም ጉተንበርግ በተዘጋጀው ቻምፒዮና በ10ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያውን መድገም ችሏል። በአቴንስ እና ሴቪላ በተካሄዱት ውድድሮችም በተመሳሳይ የወርቅ ሜዳሊያውን የግሉ አድርጓል። እአአ የ2001 የኤድመንተን ቻምፒዮና የመጀመሪያውን የነሃስ ሜዳሊያ ሲወስድ፤ በመድረኩ የመጨረሻ ተሳትፎውን ያደረገበት የፓሪሱ ቻምፒዮናም አትሌቱን በብር ሜዳሊያ ነው ያሰናበተው። አሁን ኃይሌ ራሱን ከውድድሮች ካገለለ ዓመታትን አስቆጥሯል። ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንትነት መንበሩን በቃኝ ብሎ ቢያስረክብም አገራቸውን ወክለው ለመሮጥ ከተዘጋጁ አትሌቶች ጎን አይጠፋም። በስድስት ጊዜ የዓለም ቻምፒዮና ተሞክሮውን ነገ በሚጀምረው የኳታር የዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያን ለሚወክሉ አትሌቶች እንደሚከተለው ያካፍላል። «ዓለም ቻምፒዮናን፤ በዓለም ላይ ያሉ ምርጥ አትሌቶች የሚሳተፉበት መሆኑ ለየት ያደርገዋል። በዳይመንድ ሊግ እና ሌሎች ውድድሮች ላይ የሚገኙት ጥቂቶች ሊሆኑ ይችላሉ፤ በዓለም ቻምፒዮና ግን በዓለም ላይ ‘አሉ’ የተባሉ አትሌቶች የሚሰባሰቡበት ነው»። ጠንካራ አትሌቶች\nየሚገናኙበትና የምርጦች\nምርጥ የሚመረጥበትም\nይኸው ውድድር\nበመሆኑ በአትሌቶች\nዘንድ በልዩነት\nይታያል። አትሌቶች\nሃገራቸውን የሚወክሉበት\nእንዲሁም ሃገራት\nባስመዘገቡት ውጤት በዓለም\nአቀፉ የአትሌቲክስ\nፌዴሬሽኖች ማህበር\nደረጃ የሚያገኙበት\nበመሆኑም፤ ስፖንሰር\nአድራጊ ተቋማትም\nጭምር ከፍተኛ\nትኩረት እንደሚሰጡት አንጋፋው አትሌት ይጠቁማል። ሃገሩን ወክሎ\nበጥረቱ ውጤት ካስመዘገበባቸው\nቻምፒዮናዎች ሁሉ እስካሁንም\nከትውስታው ያልተሰረዙ\nገጠመኞችም አሉት።\n«ከተካፈልኩባቸው ቻምፒዮናዎች\nሁሉ እስካሁንም\nየማዝንበት አጋጣሚ\nየደረሰው በስቱትጋርት\nነው። እአአ የ1993ቱ\nቻምፒዮና በ5ሺ\nሜትር አሸናፊነት\nአምልጦን የብር ሜዳሊያ\nነበር ያገኘነው»\nሲል ቁጭቱን\nይናገራል። ገጠመኞቹ\nእነዚህ ብቻም አይደሉም\nኃይሌ ይቀጥላል፤\n«እአአ 2001 ኤድመንተን\nላይ እኔና አሰፋ\nመዝገቡ ማሸነፍ\nበምንችለው ውድድር\nላይ የፈጸምነው\nስህተት ነው። በተለይ\nእኔ ለአምስተኛ\nጊዜ አሸናፊ\nእንደምሆን በማመኔ\nመዘናጋት አሳይቼ\nነበር፤ ባልተጠበቀ\nሁኔታ ግን አንድ\nኬንያዊ አትሌት\nአሸነፈን። ይህም እስካሁን\nእንደ እግር እሳት\nነው የሚለበልበኝ»\nበማለት በድንገት\nከመሃላቸው ፈትልኮ\nወርቁን ስላጠለቀው\nጥርሰ ፍንጭቱ\nኬንያዊ አትሌት\nቻርልስ ካማቲ ያስታውሳል። ከተካፈለባቸው ቻምፒዮናዎች ሁሉ አንጋፋውን አትሌት በተለየ የሚያስደስተው እአአ 1995 በስዊድን ጉተንበርግ የነበረው ተሳትፎ ነው። በዚህ ውድድር ላይ የመጨረሻውን 200ሜትር፤ የወቅቱ ጠንካራ አትሌቶች ከነበሩት፤ ፖል ቴርጋት፣ ካሊድ ካህ እና ሳላ ኢሱ ለማምለጥ ያደረገው ጥረት ያስደስተዋል። አጨራረሱን ሲያስታውስም ምናልባት ከ800ሜትር ሯጮች በላይ የፈጠነ እንደነበር ነው የሚገልጸው። ከትውስታው መልስም\nነገ በዶሃ በሚጀመረው\nቻምፒዮና ስለሚሳተፈው\nየኢትዮጵያ ብሄራዊ\nቡድን አስተያየት\nሰጥቷል። ከዳይመንድ\nሊግ ውድደሮች\nበመነሳት በወንድም\nበሴትም በተለይ\nበ10ሺ ሜትር\nጥሩ ጥሩ አትሌቶች\nአሉ። በዚህ ውድድር\nላይ ግን ብልጠት\nበጣም አስፈላጊ\nነገር ነው። በተለይ\nየመጨረሻዎቹ ሜትሮች\nላይ የተለየ\nነገር ካላደረጉ\nልፋታቸው ሁሉ ገደል\nነው የሚገባው።\nየመጨረሻው 100ሜትር\nቀላል አይደለም\nበጣም ብዙ ነገር\nነው የሚያበላሸው፤ በመሆኑም እዚህ ላይ አእምሯቸውንና ሰውነታቸውን መጠቀም አለባቸው። ብልጠት ካልታከለበት ሰውነት ብቻውን አሸናፊ አያደርግም፤ ብልጥ ከሆኑ ግን ሰውነትም ቢደክም ማሸነፍ ይቻላል በማለት የይቻላል ተምሳሌቱን ይናገራል። ቡድኑ ወደ ዶሃ ከመጓዙ ከሁለት ቀናት አስቀድሞም የብዙዎች ተምሳሌት የሆነው አትሌቱ ልምምድ በሚያደርጉበት አዲስ አበባ ስታዲየም ተገኝቶ ምክርና ተሞክሮውን አካፍሏል። «ውድድር ‘እንዲህ ነው፤ እንዲያ ነው’ አይባልም ሁሉም የሰራውን ነው የሚያመጣው። ስታዲየሙ የሚያቀዘቅዝ መሳሪያ ስለተገጠመለት እዚህ ካለው አየር የተለየ አይሆንም። ከዚህ ባለፈ በአትሌቶችም ሆነ አሰልጣኞች መካከል አብሮነት አስፈላጊ ነው፤ የእናንተ አብሮ መሆን ብዙ ነገር ይቀይራል። የእናንተ በጋራ መስራት ከውጤትም በላይ ነው፤ ህዝቡም የሚፈልገው ይሄንኑ ነው። ሁሌም ሩጫ ስትሮጡ መጠንቀቅ ያለባችሁ የመጨረሻዎቹን 500 እና 600ሜትሮች ነው። ሌላውን ርቀት ሳትጨናነቁና ሳትፈሩ ዘና ብላችሁ ሸፍኑ። በመካከለኛ ርቀትም ቢሆን ሩጫውን ማንበብ የግድ ነው፤ መዘናጋት አያስፈልግም» ሲልም አስገንዝቧል። ቀጥሎም፤ «አንዳችሁ ለሌላችሁ ውጤት አስፈላጊ እንደሆናችሁ እንዳትዘነጉ። ልብ አድርጉ፤ አሰልጣኞችም ሆናችሁ አትሌቶች ‘እኔ ውጤት ላምጣ እንጂ ስለሌላው አያገባኝም’ ማለት የለባችሁም። ሌላው ማስታወስ ያለባችሁ እናንተን የሚመለከቱ ብዙ ሺ ታዳጊዎች አሉ፤ ውጤት ሁለተኛ ነገር ነው ዋናው እርስ በእርሳችሁ የምታሳዩት ስነ-ምግባር ነው። እናንተ ውጤት ስላመጣችሁ ብቻ መደሰት ሳይሆን ሌላውንም መደገፍ በተመሳሳይ አስፈላጊ ነገር ነው። አሰልጣኞች፣ የቡድን መሪዎችና ቴራፒስቶችም ከልምምዱ ባሻገር ስነ-ምግባር ላይም ማተኮር አለባችሁ»ም ብሏል። በመጨረሻም ለብሄራዊ ቡድኑ መልካም ውድድር እንዲሆን ተመኝቷል።አዲስ ዘመን  መስከረም 15/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "50f62ba170ff10bda28e8097fbd8bf73" }, { "passage": "በአትሌቲክሱ ዓለም\nረጅም ርቀት ውድድሮች\nየስፖርቱ ድምቀቶች ናቸው።\nበተለይም አምስትና አስር\nሺ ሜትር ውድድሮች\nበዓለም ላይ ከፍተኛ\nተቀባይነትን እያገኙ ለመጡ\nየማራቶን ውድድሮች መሰረት\nናቸው። እንደ አጠቃላይ\nለአትሌቲክስ ስፖርትም ቢሆን\nየጀርባ አጥንቶች ናቸው።\nበታላቁ የስፖርት መድረክ\nኦሊምፒክም ቢሆን የረጅም\nርቀት ውድድሮች የማይረሳ\nታሪክ ያላቸውና ከስፖርት\nቤተሰቡ ምናብ ወደ\nፊትም ቢሆን የማይፋቁ\nናቸው።እአአ 2000 ሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ\nጀግናው አትሌት ኃይሌ\nገብረስላሴና ኬንያዊው ድንቅ\nአትሌት ፖል ቴርጋት\nበአስር ሺ ሜትር\nቁጭ ብድግ የሚያደርግ\nግሩም ፉክክር ማን\nይረሳዋል? ይህን ከህሊና\nየማይፋቅ ውድድር ጨምሮ\nበርካታ የአምስትና አስር\nሺ ሜትር ውድድሮች\nየኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና\nመገለጫዎች መሆናቸውን የሚክድ\nይኖራል ብሎ ማሰብ\nከባድ ነው። በእነዚህ\nውድድሮች ላይ ምሥራቅ\nአፍሪካውያን ፍፁም የበላይነት\nእየጎላ መምጣቱም ለምዕራባውያን ምቾት እንዳልሰጣቸው ምልክቶች መታየት\nየጀመሩት ዛሬ አይደለም።\nለዚህም ጠንክረው ሠርተው\nየበላይነት ከመያዝ ይልቅ\nበሴራ ለማመናቸው በርካታ\nማሳያዎችን ማስቀመጥ ይቻላል።\nእኛ ብቻ በሁሉም\nነገር የበላይ እንሁን\nየሚል ክፉ አባዜ\nየተጠናወታቸው ምዕራባውያን በመጀመሪያ\nየአገር አቋራጭ ሩጫን\nከኦሊምፒክ ድራሹ እንዲጠፋ\nአደረጉ። ቀጥሎም ቀስበቀስ\nየአስር ሺ ሜትር\nየመም(ትራክ) ውድድሮችን\nከገበያ ጋር በማስተሳሰር ‹‹አዋጭ አይደሉም››\nበሚል በዓመት አንድ\nጊዜ እንኳን የሚካሄዱበትን መንገድ ጥርቅም\nአድርገው ዘጉ። በዚህም\nበርካታ የምሥራቅ አፍሪካ\nአትሌቶች በለጋ ዕድሜያቸው\nፊታቸውን ወደ ጎዳናና\nማራቶን ውድድሮች አዙረው\nሮጠው ሳይጠግቡ ከፉክክር\nውጪ እንዲሆኑ አደረጉ።\nየምሥራቅ አፍሪካ አትሌቶች\nአስር ሺ ሜትርን\nእርግፍ አድርገው በጎዳና\nውድድር በተጠመዱበትና በተዘናጉበት ወቅት ግን\nየቤት ሥራቸውን ውስጥ\nለውስጥ ሠርተው በሞፋራህና\nበጋለን ሩፕ አማካኝነት\nስንት የኦሊምፒክና የዓለም\nቻምፒዮና ሜዳሊያዎችን እንደሰበሰቡ የምንዘነጋው አይደለም።\nየሞፋራህና ጋለን ሩፕ\nየጀግንነት ጀምበር እየጠለቀ\nሲመጣም ችላ ብለውት\nየቆየውን አምስትና አስር\nሺ ሜትር ከኦሊምፒክ\nየማስወጣት አጀንዳ ዳግም\nአራገቡት። ‹‹ውጣ አትበለው\nእንዲወጣ አድርገው›› እንደሚባለው አስር ሺ\nሜትርን እንዳኮላሹት ሁሉ\nየቀራቸውን አምስት ሺ\nሜትር ውድድርን ለመቅበር\nከሰሞኑ ሌላ ስልት\nይዘው ከች ብለዋል።\nየዓለም አቀፉ አትሌቲክስ\nፌዴሬ ሽኖች ማህበር\n(አይ.ኤኤ.ኤፍ)\nባለፈው ማክሰኞ ኳታር\nዶሃ ላይ አምስት\nሺ ሜትር ውድድር\nከ2020 ጀምሮ ከዳይመንድ\nሊግ ፉክክሮች እንዲሰረዙ\nወስኗል። ይህ ውሳኔ\nአምስት ሺ ሜትር\nየአስር ሺ ሜትር\nዕጣ ፋንታ እንዲደርሰው የሚያደርግ በመሆኑ\nከአፍሪካውያን የስፖርት ቤተሰቦች\nተቃውሞና ወቀሳ እየቀረበበትም ይገኛል። የኢትዮጵያና ኬንያ አትሌቲክስ\nፌዴሬ ሽኖችን ጨምሮ\nጀግናው አትሌት ኃይሌ\nገብረስላሴ ውሳኔውን ከተቃወሙት\nመካከል ይገኙበታል። ባለፉት\nሁለት ቀናትም አንዳንድ\nየጃማይካ የቀድሞ አትሌቶች\nድምፃቸውን ማሰማት ጀምረዋል።\nይህ ውሳኔ አፍሪካ\nበዓለም አቀፉ አትሌቲክስ\nፌዴሬሽኖች ማህበር ተሰሚ\nየሆነ ወካይ እንደሌላት\nአሳይቶናል። ያም ቢሆን\nረጅም ርቀት ውድድሮች\nየበለጠ አፍሪካውያንን ተጠቃሚ\nየሚያደርጉ በመሆኑ የአፍሪካ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር\n(ሲ ኤኤ)፤\nየአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ(አኖካ) ውሳኔውን ለማስቀየር\nአልረፈደባቸውም። የአበበ ቢቂላ ታሪካዊ\nድል የኢትዮ ጵያውያን\nብቻ እንዳልሆነው ሁሉ\nይህ ጉዳይ የምሥራቅ\nአፍሪካውያኑ ጎረቤታሞች ብቻ\nአይደለም። አፍሪካውያን በታላቁ\nየኦሊምፒክ መድረክ ሰንደቅ\nዓላማቸው ከፍ ብሎ\nሲውለበለብ፣ ብሔራዊ መዝሙራቸው\nበክብር ሲዘመር ማየት\nከፈለጉ ይህን ውሳኔ\nለማስቀየር በአንድ ላይ\nመቆም አለባቸው። ረጅም ርቀት የአፍሪካውያን ታሪክ በወርቅ\nቀለም የተፃፈበት ዛሬም\nነገም መገለጫቸው ሆኖ\nየሚኖር ህልውናቸው ነው።\nእንደ ኃይሌ ሁሉ\nሌሎች ተፅዕኖ ፈጣሪ\nአፍሪካውያን አትሌቶች ድምፃቸውን\nማሰማት ይኖርባቸዋል። በኬንያዊው\nድንቅ አትሌት ፖል\nቴርጋት የሚመራው የአፍሪካ\nአትሌቶች ኮሚሽንም እዚህ\nጋር አቅሙን ማሳየት\nአለበት።ምዕራባውያኑ እንዲህ ዓይነቱ\nአጋጣሚ በራሳቸው ላይ\nእንዲደርስ ማድረግ አይደለም\nበኦሊምፒክ እንዲስፋፋና የበላይነታቸውን ይዘው እንዲዘልቁ\nያገኙትን ዕድል ከመጠቀም\nወደኋላ አይሉም። አሁንም\nበቀጣዩ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ እንኳን የነሱ\nፍላጎት ያለባቸው ወይም\nሜዳሊያ ያስገኝልናል ብለው\nያሰቡትን ማንኛውንም እንቅስቃሴ\nየኦሊምፒክ ስፖርት እንዲሆን\nእያደረጉ ነው።በቀጣዩ ኦሊምፒክ ብሬክ\nዳንስ ሳይቀር እንዲካተት\nአድርገዋል። አፍሪካውያንም ከምዕራባውያን ጋር በኦሊምፒክ\nተፎካካሪ ሆነው ለመገኘት\nእንደ አገር አቋራጭ\nሩጫ ዓይነት ውድድሮችን\nከመጠቀም ባለፈ ረጅም\nርቀቶች ላይ ያንዣበበውን አደጋ ለማስቀረት\nበጋራ መጋፈጥ ግድ\nይላቸዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንትና የቀድሞ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የኦሊምፒክ አሸናፊ እንግሊዛዊው ሴባስቲያን ኮ ወደ ስልጣን ሲመጡ እዚሁ አዲስ አበባ ላይ የረጅም ርቀት የቀድሞ ዝናና ስም ለመመለስ እንደሚሠሩ ቃል ቢገቡም አሁን ቃላቸውን አጥፈዋል። አፍሪካውያን በአንድነት ካሁኑ ካልታገሉም እንደ አገር አቀራጭ ውድድር ሁሉ አስርና አምስት ሺ ሜትር ውድድሮች በቅርቡ ከኦሊምፒክ ላለመሰረዛቸው እርግጠኛ መሆን አይቻልም።አዲስ ዘመን\nመጋቢት 6 /2011ቦጋለ\nአበበ ", "passage_id": "6d6589aa4c0a66d90450b044e54ca629" }, { "passage": "ቦጋለ አበበበኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ለበርካታ ወራት ተቋርጠው የቆዩ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች ካለፈው ሐምሌ መጨረሻ ጀምሮ በሂደት ወደ መደበኛ መርሃግብራቸው እየተመለሱ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ውድድሮች በተመለሱበት ጥቂት ወራትም በተለይም የረጅም ርቀት የዓለም ክብረወሰኖች ለማመን በሚቸግር መልኩ ሲሰበሩ እየተስተዋለ ይገኛል፡፡ ይህም የስፖርቱን አፍቃሪዎች ከማነጋገሩ ባሻገር ተንታኞች ጭምር ግራ እንዲጋቡ ያደረገ ክስተት ሆኗል፡፡ በተለይም የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰን ከወረርሽኙ በፊትም ቢሆን ከሌሎች ርቀቶች በተለየ በሁለቱም ፆታ በተደጋጋሚ ሲሰበር መስተዋሉ አነጋጋሪ አድርጎታል፡፡ የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰን በዓለም አትሌቲክስ እኤአ ከ2004 አንስቶ እውቅና እየተሰጠው ከመጣ ወዲህ በወንዶች አምስትና በሴቶች ስድስት የዓለም ክብረወሰኖች ተመዝግበዋል፡፡ ከዚህ ዓመት በፊት በርቀቱ የተመዘገቡ ሰዓቶች በዓለም አትሌቲክስ ‹‹የዓለም ፈጣን ሰዓት›› በሚል ይታወቅ ነበር፡፡ የወንዶች ግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰን ባለፈው እሁድ በቫሌንሲያ የተመዘገበ ሲሆን ኬንያዊው አትሌት ኪቢዎት ኬንዲ 57፡32 በሆነ ሰዓት የክብረወሰኑ ባለቤት ሆኗል::የሴቶቹ ደግሞ ባለፈው የካቲት በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የራስ አል ኪማህ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አባብል የሻነህ በ1፡04፡31 በሆነ ሰዓት ያስመዘገበችው ነው፡፡ ይህም በጥቅምት 2017 ኬንያዊቷ ጆይስሊን ጂፕኮስጌ በቫሌንሲያ ግማሽ ማራቶን ካስመዘገበችው የቀድሞው የዓለም ክብረወሰን በሃያ ሰከንድ የተሻለ ነበር፡፡ በመስከረም 2019 ሌላኛዋ  ኬንያዊት\nብሪጊድ ኮስጌ በኒውካስትል ታላቁ\nሩጫ 64፡28 በሆነ ሰዓት\nከቀድሞው ክብረወሰን በሃያ ሦስት\nሰከንድ የተሻለ ፈጣን ሰዓት\nብታስመዘግብም የዓለም አትሌቲክስ ለክብረወሰኑ\nእውቅና አልሰጠውም። እኤአ ከ2011 ጀምሮ\nየዓለም አትሌቲክስ የሴቶች ግማሽ\nማራቶን ክብረወሰኖችን በሴትና በወንድ አሯሯጭ\nየተመዘገቡ ብሎ በሁለት ከፍሏቸዋል።  በሴት\nአሯሯጮች የተመዘገበው የርቀቱ ክብረወሰንም በኬንያዊቷ\nአትሌት ፔርስ ጂፕቺርቺር 1፡05፡16 በሆነ ሰዓት\nከወር በፊት በፖላንድ ጊዲኒያ\nየዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና\nየተመዘገበ ነው። ባለፈው ሐምሌ መጨረሻ ለአስራ ስድስት ዓመታት ያልተደፈረው የቀነኒሳ በቀለ የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን በዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሞናኮ ላይ ከተሰበረ ወዲህ የዓለም ክብረወሰኖች በተለይም በረጅም ርቀት ውድድሮች እንደልብ የሚሰበሩ ሆነዋል። ከዩጋዳዊው ያልተጠበቀ ክብረወሰን በኋላ አንድ ወር ባልሞላ ልዩነት ትውልደ ሶማሊያዊው የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ እኤአ 2007 ላይ በጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ተይዞ የቆየው ‹የአንድ ሰዓት ውድድር› የዓለም ክብረወሰን ብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ላይ ከ21፡330 ወደ 21፡285 ተሻሽሏል። በተመሳሳይ ርቀት እንዲሁም በተመሳሳይ ቀንና ውድድር በኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድሬ ቱኔ 18፡930 ተይዞ የቆየው የዓለም ክብረወሰን በትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን 18፡517 በሆነ ሰዓት ተሻሽሏል። የሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአንድ ሰዓት ውድድር የዓለም ክብረወሰኖች በተሰበሩ በአንድ ወር ልዩነት ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ለአስራ አምስት ዓመታት ያልተደፈረውን የቀነኒሳ በቀለ የአስር ሺ ሜትር ክብረወሰን በ6፡53 ሰከንድ መስበር ችሏል። በተመሳሳይ ቀን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌትና የረጅም ርቀት ንግስት ጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት ተይዞ ሳይሰበር የቆየውን የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን 14፡06 በሆነ ሰዓት ሰብራዋለች። ኬንያውያን አትሌቶችም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኋላ ባንሰራራው የአትሌቲክስ ውድድር የክብረወሰን ተቋዳሽ ናቸው። ለዚህም በዓለም ግማሽ ማራቶን በአርባ ሁለት ቀናት ልዩነት ሁለት የዓለም ክብረወሰኖችን የጨበጠችው ኬንያዊቷ ፔስር ጂፕቺርቺር ትክክለኛ ማሳይ ናት። መስከረም ላይ በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን የሴቶችን ብቻ የርቀቱን የዓለም ክብረወሰን በ1፡05፡24 ሰዓት ያሻሻለችው ኬንያዊት አትሌት ከአርባ ሁለት ቀናት በኋላ በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የራሷን ክብረወሰን በአስራ ስምንት ሰከንድ ማሻሻል ችላለች። እነዚህ ሁሉ ክብረወሰኖች ሲሰባበሩና አትሌቶች በተለየ መልኩ አስደናቂ ብቃት ሲያሳዩ አብዛኛው የስፖርት ቤተሰብ ሁለት ነገሮችን ጠርጥሯል። ይህም በወረርሽኙ ምክንያት አትሌቶች ለረጅም ጊዜ ከውድድር በመራቃቸው ሰፊ የዝግጅት ጊዜ በማግኘት ወደ ውድድር ሲመለሱ ምርጥ ብቃት ሊኖራቸው እንደቻለና በነዚያ የረፍት ጊዜያት በጉዳት ላይ የነበሩ አትሌቶች በበቂ ሁኔታ ማገገም በመቻላቸው እንደሆነ ይታሰባል። ስፖርቱን በጥልቀት የሚመለከቱ በርካታ ተንታኞች ግን ከዚህም የበለጡ ገፊ ምክንያቶች ከክብረወሰኖቹ መሰባበር ጀርባ እንዳሉ ያምናሉ። የልምምድ ስነልቦናና ሂደት በወረርሽኙ ምክንያት እየተለወጠ መምጣቱ ለክብረወሰኖቹ መሻሻል አንድ ምክንያት ተደርጎ ይወሰዳል። ይህም የወረርሽኙ ስጋት ቀደም ብሎ አትሌቶች በርከት ብለው በአንድ አሰልጣኝና በአንድ ካምፕ ውስጥ ሆነው የሚያደርጉትን የተለመደ ዝግጅት ወደ ጎን ትተው በተናጠል በሚመቻቸው ስፍራና በቤታቸው ሆነው እንዲዘጋጁ እድል መስጠቱ ነው። ይህ አጋጣሚ አትሌቶች አንዱ አንዱን ሳይጠብቅ በራሳቸው መርሃግብር መሰረት ወጥ በሆነ መልኩ እስከ አቅማቸው ጥግ ድረስ እንዲዘጋጁ ያስቻላቸው ሲሆን በስነልቦናውም ረገድ ጠንካራ እንዲሆኑ አድርጓል። ለዚህም ከወረርሽኙ በኋላ ክብረወሰኖችን ያሻሻሉ አትሌቶች ቀደም ሲል ይከተሉት የነበረው የልምምድ መልክ በወረርሽኙ ሳቢያ መቀየሩ ለክብረወሰኖች መሻሻል ቁልፍ ሚና እንዳለው የሚያስቀምጡ ባለሙያዎች በርካታ ናቸው። በሌላ መልኩ አትሌቶች በወረርሽኝ ምክንያት ውድድሮች ቢቆሙም የሆነ ጊዜ ላይ እንደሚቀጥሉ አውቀው ዝግጅታቸውን ሳያቋርጡ ተግተው መስራታቸው የክብረወሰን ባለቤት እንዳደረጋቸው ይታመናል። አትሌቶች ወረርሽኙ የጤና ስጋት ቢሆንም መጥፎን አጋጣሚ ወደ ጥሩ ለውጠው ተጠቅመዋል። አቋማቸው እንዳይወርድ በመጠንቀቅ መዘጋጀታቸው ኋላ ላይ ለስኬት አብቅቷቸዋል። በተለይም እቤት የመቀመጥ አስገዳጅ ሁኔታው ቀደም ሲል የነበረባቸውን የተጣበበ የልምምድና የውድድር ጫና በማስቀረቱ በበቂ ሁኔታ እንዲዘጋጁ በር ስለከፈተላቸው በደህናው ጊዜ ማሳካት ያልቻሉትን ክብረወሰን እንዲያሳኩ አድርጓቸዋል። ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ መልካም አጋጣሚዎች እንዳሉ ሆነው የስፖርት ቴክኖሎጂ እየዘመነ መምጣት ለተመዘገቡት ክብረወሰኖች የአንበሳውን ድርሻ እንደሚይዝም ዓለም አቀፍ የስፖርቱ ምሁራን የሚስማሙበት ጉዳይ ነው። ባለፉት ጥቂት ወራት ሲመዘገቡ ያየናቸው በርካታ ክብረወሰኖች አትሌቶች የሚያስመዘግቧቸው ሰዓቶች ላይ ሰፊ ልዩነት በሚፈጥሩ ዘመናዊ የመሮጫ ጫማ እንዲሁም አሯሯጮች በተለይም በመም ውድድሮች ከሰው ይልቅ ቴክኖሎጂ ሆኖ አትሌቶችን እስከ መጨረሻ ድረስ በሚፈለገው ደረጃ በማገዝ የተመዘገቡ ናቸው። ግዙፉ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚያቀርባቸው የመሮጫ ጫማዎች ቀደም ሲል የዓለም ክብረወሰን ሲመዘገብባቸው ከቆዩ የመሮጫ ጫማዎች አንፃር በአትሌቶች ፍጥነት ላይ የጎላ ተፅዕኖ እንዳላቸው አትሌቶችም ይሁን የስፖርት ቤተሰቡ ይስማማሉ። ከዚህ በላይ የጥሩነሽ ዲባባ የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ለተሰንበት ግደይ እና የቀነኒሳ በቀለ የአምስትና አስር ሺ ሜትር ክብረወሰኖች በዩጋዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሲሰበሩ አትሌቶቹን በአሯሯጭነት ያገዛቸው በመሮጫው መም ዙሪያ የተገጠመው መብራት(Wave-lights) እንደነበር ይታወቃል። ይህ ቴክኖሎጂ አትሌቶቹ በምን ያህል ፍጥነት እያንዳንዱን ዙር ሮጠው ክብረወሰን እንደሚጨብጡ አስልቶ በማሯሯጥ እስከ መጨረሻ ድረስ ደግፏቸዋል። አሯሯጭ በአትሌቲክሱ ዓለም ክብረወሰኖችን ለማስመዝገብ ወሳኙ ነገር እንደሆነ ይታወቃል። አንዳንድ ጊዜ ሴት አትሌቶች በወንድ አሯሯጮች ታግዘውም አሯሯጮች በሚፈለገው ፍጥነት መጓዝ ካልቻሉ ክብረወሰን የማይሰበርበት አጋጣሚ ጥቂት እንዳልሆነ ይታወቃል። አሯሯጩ ቴክኖሎጂ ሆኖ እስከ መጨረሻ ድረስ ወጥ በሆነ ስሌት አትሌቶችን ሲያግዝ ግን የተለየ እንደሚሆን የቅርቦቹ ክብረወሰኖች ምስክር ናቸው።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 5/2013 ", "passage_id": "bd9d938962843a2319cf059722b904bd" }, { "passage": "ይህ ወቅት በአትሌቲክስ ስፖርት የአገር አቋራጭ ውድድሮች በብዛት የሚካሄዱበት ነው። ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻም በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የነሐስ ደረጃ የተሰጠው የቫሌንሺያ አገር አቋራጭ ውድድር ተካሂዷል። በውድድሩም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ ክብረወሰን በመሰባበርም ጭምር አሸናፊ ሆነዋል።በስፔን ዋና ከተማ በተካሄደው በዚህ ውድድር13ሺ ሯጮች ተሳትፈውበታል። 11ሺ የሚሆኑትም የ10ኪሎ ሜትሩን የመጨረሻ መስመር መርገጥ ችለዋል። እጅግ ብርዳማ በነበረው ጠዋት የተጀመረው የሴቶቹ ውድድር ሊሟሟቅ የቻለው በኢትዮጵያዊቷ እና ኬንያዊቷ አትሌት መካከል በነበረው ፉክክር ነው።አትሌት ጸሐይ ገመቹ ከስምንተኛው ኪሎ ሜትር በኋላ ኬንያዊቷን ግሎሪያ ኬትን ጥላት በመሮጥም 30ደቂቃ ከ15ሰከንድ በሆነ ሰዓት የመጨረሻዋን መስመር በመርገጥ አሸናፊነቷን ማረጋገጥ ችላለች። አትሌቷ በአስቸጋሪው የአየር ሁኔታ የገባችበት ሰዓትም የርቀቱን የኢትዮጵያ ክብረወሰን በ15ሰከንዶች ያሻሻለ ሆኗል። አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ርቀቱን 30 ደቂቃ30 በመግባት ለዓመታት ክብረወሰኑን የግሏ አድርጋ ነበር የቆየችው።ፈጣን በነበረው ውድድር እስከ አራት ያለውን ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁት አትሌቶች በሰከንዶች ብቻ በመበላለጥ ከ31ደቂቃ በታች ነበር የሮጡት። የኢትዮጵያዊቷ አትሌት ብርቱ ተፎካካሪ የነበረችው ኬንያዊቷ ግሎሪያ ኬት በበኩሏ በሰከንዶች ዘግይታ 30:26 በሆነ ሰዓት ውድድሩን ለማጠናቀቅ ችላለች። ኬንያውያኑ አትሌቶች ኢቫሊን ቺርቺር እና ሮስመሪ ዋንጂሩ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ ሲይዙ፤ 30:43 እና30:50 ደግሞ የገቡበት ሰዓት ነው። በውድድሩ የተካፈለችው ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሁነኛው ይስማን ደግሞ ስድስተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሯን አጠናቃለች።በወንዶች በኩል በተካሄደው ውድድር አሸናፊ የሆነው ኢትዮጵያዊው አትሌት ጫላ ከተማ የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻልም ጭምር ድርብ ክብር አግኝቷል። በአንድ ኪሎ ሜትር 2ደቂቃ ከ43 እና 2ደቂቃ ከ45 ሰከንድ በተሮጠው በዚህ ውድድር ላይ፤ የምስራቅ አፍሪካዎቹ አትሌቶች በመምራት ተጽዕኖ አሳድረው ነበር። ጫላ ከተማ፣ አባይነህ ደጉ እና በተስፋ ጌታሁን ኢትዮጵያን ወክለው፣ በኬንያ በኩል ማቲው ኮፕኮሪር፣ ኤድዋርድ ኪበት፣ ቪዲች ቺሩዮች እንዲሁም በኡጋንዳ በኩል ስቴፈን ኪሳ ከፍተኛ የአሸናፊነት ፉክክር ሲያደርጉ የነበሩ አትሌቶች ናቸው። የርቀቱ አጋማሽ 13ደቂቃ ከ43 ሰከንዶች በሆነ ሰዓት የተሸፈነ ሲሆን፤ ይህም የቦታው የተመዘገበ ፈጣን ሰዓት ነው።ርቀቱን ለማጠቃለል 200ሜትሮች ሲቀሩትም ኢትዮጵያዊው አትሌት ጫላ ከተማ አፈትልኮ በመውጣት27ደቂቃ ከ23ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ የቦታውን ክብረወሰን ጨብጧል። የከዚህ ቀደሙ ክብረወሰን የተያዘው በዓለም ሻምፒዮኑ ማርቲን ፊዝ በገባበት31:36 በሆነ ሰዓትም ነበር። ኡጋንዳዊው ስቴፈን ኪሳ በበኩሉ በአንድ ሰከንድ ልዩነት 27:24 ከመጨረሻው ሊደርስ ችሏል። ኬንያዊው ቪዲች ቺሩዮች 27:26 በሆነ ሰዓት የነሐስ ሜዳሊያ ሲያገኝ፤ ኢትዮጵያዊው በተስፋ ጌታሁን ደግሞ 27:39 በሆነ ሰዓት አራተኛ ሆኗል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አባይነህ ደጉ ሰባተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ፈጽሟል።አዲስ ዘመን ጥር 7/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "0df1614d0e2efe72c3c4d9e759bb35a2" }, { "passage": "ከዓምናው የዓለም ሻምፒዮና የ10,000 ሜትር ሁለተኝነቷ በኋላ፣  ለተሰንበት ግደይ በ5,000 ሜትር የመም (ትራክ) ላይ ሩጫ የምንጊዜውም እጅግ ፈጣኗ ሴት ሆናለች። ኢትዮጵያዊቷ ለሰንበት፣ ረቡዕ ጥቅምት 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ባደረገችው አስደናቂ ሩጫ ለ12 ዓመታት በጥሩነሽ ዲባባ ተይዞ የነበረውን በስፔን ቫሌንሽያ ከተማ፣ በ14:06.62  በመሮጥ ነው የዓለምን ክብረወሰን መስበር የቻለችው። ይህ ድንቅ ክንዋኔዋ ነው በጥሩነሽ ዲባባ በ2008 በ14:11.15 ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን ለመስበር የበቃችው።ኦሊምፒክ ቻነልና ራነርስ ወርልድ እንደዘገቡት የመጨረሻዎቹን አምስት ዙሮች ብቻዋን የሮጠችው ለተሰንበት፣ ከውድድሩ ፍጻሜ በኋላ \"ይህ የረዥም ጊዜ ሕልሜ ነው፤ በውድድሩም በጣም ተደስቻለሁ!\" ብላለች።  \"ይህ በጣም ግሩም ነው፡፡ ከዚህ በፊት ጥሩነሽ ዲባባ ሰበረች፤ አሁን ደግሞ እኔ፡፡” ስትልም አክላለች። የ5,000 ሜትር የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር የኢትዮጵያውያን ሯጮች የፈጣን ሯጭነት ውርስን የ22 ዓመቷ ለተሰንበት አስቀጥላለች።ሌላው የምሽቱ ተጨማሪ  የክብረ ወሰን አስደናቂ ክስተት በቀነኒሳ በቀለ በ26:17.53  ለ15 ዓመታት ተይዞ የነበረው የ10,000 ሜትር ሪከርድን ዑጋንዳዊው ጆሹዋ ቼፕቴጊ በ26:11.02 በመፈጸም መስበሩ ነው። ባለፈው ነሐሴ በተደረገው ዳይመንድ ሊግ በ5000 ሜትርም የቀነኒሳን የዓለም ሪከርድ መስበሩም ይታወሳል፡፡", "passage_id": "d7533a78252bfbdc1d1f94a4b4fa4a46" } ]
838989e7421e5760de7c02511e99ce26
b9c3e896b5df99260852ab7f5f8717a3
”በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አካባቢ የተፈጠረው የጸጥታ ችግር ከተሳሳተ ግምት የመነጨ ነው” – አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
ዋቅሹም ፍቃዱአዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አካባቢ የተስተዋለው የፀጥታ ችግር በተወሰኑ የሱዳን ሚሊሻዎች እና ጥቂት ወታደሮች የተሳሳተ ግምት በመነጨ በድንበር አካባቢ ተኩስ በመክፈታቸው ምክንያት የተፈጠረ እንደነበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ። አምባሳደር ዲና በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የህወሓት ጁንታ በመከላከያ ሠራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ መንግሥት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ህግ የማስከበር ሥራ ላይ ባለበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጰያ በድንበር አካባቢ ትኩረት አይሰጥም በሚል የተሳሳተ ግምት የተወሰኑ የሱዳን ሚሊሻዎች እና ጥቂት ወታደሮች የተሳሳተ ግምት በመነጨ በድንበር አካባቢ ተኩስ ከፍተዋል። ይሁን እንጂ መንግሥት ሙሉ ትኩረቱን በሰሜን የህግ ማስከበር ላይ ቢያደርግም በድንበር አካባቢም የጸጥታ ችግር እንዳይከሰት በትኩረት እየሠራ መሆኑን የገለጹት አምባሳደር ዲና፤ በድንበር አካባቢ ያሉ የሱዳን ሀይሎች ግን “የኢትዮጵያ መንግሥት በድንበር አካባቢ ትኩረት አይስጥም” በማለት በተሳሳተ ግምት የድንበር አካባቢ ህዝባችን ለማጥቃት ተኩስ የከፈቱ ቢሆንም በመከላከያ ሠራዊትና በአካባቢው ሚሊሻ እንደ ተመከቱ ተናግረዋል። የደረሰ ጉዳት ካለም የጉዳቱ መጠን ለወደፊት ተጣርቶ የሚገለጽ ይሆናል ብለዋል። እንደ አምባሳደር ዲና ገለጻ፤ ግጭቱ የሁለቱም አገራትም መሪዎችም ፍላጎት አይደለም። የኢትዮጵያ መንግሥትም ጉዳዩን አስመልክቶ ከሱዳን ጋር ተነጋግሯል። በቀጣይም በአካባቢው አልፎ አልፎ ለሚከሰተው ችግር መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ዘላቂ እልባት እንዲያገኝ ይሰራል። የተጀመረው የህግ ማስከበር ስራም በአጭር ጊዜ ውስጥ ስለተጠናቀቀ ወንጀለኞችንም አድኖ ለመያዝ ከሱዳን መንግሥት ጋር በቅርበት እየሰራ ይገኛል። በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖርና አርሶ አደሩ ምርቱን በአግባቡ እንዳይሰበስብ ፍላጎታቸውን በትርምስ ለማሳካት የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች በርካታ መሆናቸውን የገለጹት አምባሳደር ዲና፤ ኢትዮጵያ ግን የሁለቱም አገራት ዘላቂ ጥቅሞች በሚያስከብር መልኩ ከሰዳን ጋር እንደምትሰራ፣ እየሰራችም እንደ ሆነ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ ሰሞኑን ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት “የተፈጠረውን ችግር ለማባባስ የሚጥሩ ኃይሎች፣ የኢትዮጵያና የሱዳን ታሪካዊ ትስስር ካለማወቅና ችግሮቻቸውን በድርድር ሲፈቱ መቆየታቸው ካለመገንዘባቸው የተነሳ ነው” ማለታቸው አይዘነጋም።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37691
[ { "passage": "ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር አልፋ በመግባት የአለም አቀፍ ህግ መጣሷን  የኢትዮ-ሱዳን የጋራ ድንበር ኮሚሽን ኮሚቴ አባል አምባሳደር ኢብራሂም እንድሪስ አስታውቀዋል፡፡በኢትዮጵያ በኩል የተወከሉት  የኢትዮ-ሱዳን የጋራ ድንበር  ኮሚሽን ኮሚቴ አባላት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የድንበር ኮሚሽን ኮሚቴ አባል አምባሳደር ኢብራሂም እንድሪስ የሱዳን ድርጊት የሀገራቱን የቀደመ ታሪክ የማይመጥን መሆኑን ገልጸው፣ ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሱዳን ጦር ከኢትዮጵያ ክልል ውስጥ በፍጥነት ለቆ ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡በዚህ ግጭት ተጎጂዎቹ ሁለቱ ሀገራት በመሆናቸው ለውጪ ጣልቃ ገብነት እድል መክፈት እንደሌለባቸውም ተጠቁሟል፡፡እ.ኤ.አ በ1972 ሁለቱ ሀገራት በመንግስታቸው ተቀባይነት ያለው የድንበር ማካለል ስራ እስኪሰራ ድረስ ነባራዊ ሁኔታ ተከብሮ እንዲቆይ ተስማምተው እንደነበር አስታውሰው፣ አሁን ላይ የሁለቱ ሀገራት የጋራ የድንበር ኮሚሽን የሀገራቱን የድንበር ጉዳይ እልባት ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ባለበት ወቅት የሱዳን ጦር ድንበር አልፎ ኢትዮጵያ መግባቱ አለም አቀፍ ህግን መጣስ ነው ብለዋል፡፡የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ውዝግብ 100 አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግስት በሀገራቱ መካከል የተለያዩ ስምምነቶች ተደርገው እ.ኤ.አ በ1903 ጉዊን በተባለ እንግሊዛዊ ሰርቬየር የሀገራቱ የጋራ ድንበር ተከልሎ እንደነበርና ኢትዮጵያ ከእውቅናዬ ውጪ ነው በሚል ምክንያት ስላልተቀበለችው በተደጋጋሚ በሁለቱ ሀገራት መካከል የድንበር ውዝግብ ሲካሄድ ቆይቷል፡፡ሀገራቱ እ.ኤ.አ በ1972 የማስተወሻ ልውውጥን በመፈራረም የጋራ ድንበራቸውን ለማካለል የተስማሙ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ሱዳን ስምምነቱን በመተው ጦሯን የኢትዮጵያን ድንበር አሳልፋ አስገብታለች፡፡(በመስከረም ቸርነት)", "passage_id": "bd8456cb93536c2720897a72bef197a2" }, { "passage": "እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ ኢትዮጵያና ሱዳን በድንበር ዙሪያ የገጠማቸውን ችግር በሰከነና በሰላማዊ መንገድ ሊፈቱት እንደሚገባ የኢትዮ- ሱዳን የድንበር ኮሚሽን አስታወቀ። የድንበር ኮሚሽን በአምባሳደር ኢብራሂም ኢድሪስ አማካይነት በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የድንበር ችግር ከዚህ ቀደም በነበሩት ስምምነቶች አማካይነት ዓለም አቀፍ ህግን ተከትሎ ሊፈታ ይገባል። አገሮቹ የገጠማቸውን ችግር በሰላማዊና በሰከነ መንገድ በውይይት ለመፍታት መጣር አለባቸው። በቅርቡ የድንበሩን ጉዳይ በተመለከተ የሁለቱም አገራት ከፍተኛ የፖለቲካ ኮሚቴ በካርቱም ሱዳን ተገናኝተው መወያየታቸውን የጠቆሙት አምባሳደር ኢብራሂም፤ ቀጣይ ስብሰባውም አዲስ አበባ ላይ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። የድንበሩ ጉዳይ ዘላቂ መፍትሄ የሚያገኘው በሀገራቱ ስምምነት እንጂ በአንድ ወገን ውሳኔ እንደማይሆን አመልክተዋል።ሁለቱ አገራት በመካከላቸው እ.ኤ.አ በ1972 የተፈረመ የማስታወሻ ልውውጥ መኖሩን ጠቁመው፤ ይህ ደግሞ ከእርሻና ሰፈራ ጋር ተያይዞ ያለውን ችግር የጋራ ልዩ ኮሚቴው በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት እንዲፈታ ያግዛል ብለዋል። በዚህ ማስታወሻ ልውውጥ መሰረት ከመፍትሔ ላይ ባለመደረሱ ድንበሩ እስከ አሁን ሊከለል አለመቻሉን ጠቁመዋል። ከዚህ አንጻር በሰሜን ዳግሊሽ ተራራ የድንበሩ ክፍል የሰፈራና የእርሻ አካባቢዎችን በተመለከተ በሁለቱም አገራት መንግስታት ተቀባይነት ያለው የመጨረሻ መፍትሔ እስካልተገኘ ድረስ አሁን ባሉበት ሁኔታና ተጨባጭ ይዞታዎች በቦታው ላይ ይቆያሉ ብለዋል ። የማስታወሻ ልውውጡም ይህንን እንደሚያስገድድ አስታውቀዋል።በቅርቡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በሰሜኒቱ የአገሪቱ ክፍል ህግ ለማስከበር መሰማራቱን ተከትሎ የሱዳን ጦር በሰሜን ዳግሊሽ አካባቢ ያለውን ድንበር ጥሶ በመግባት ነባራዊ ሁኔታውን አደጋ ላይ ጥሏል ያሉት አምባሳደር ኢብራሂም፣ ከዛን ጊዜ ጀምሮም ከባድ መሳሪያን ሳይቀር በመጠቀም የተደራጁ ጥቃቶችን ፈጽሟል ብለዋል። አርሶ አደሮችን߹ የግብርና መሳሪያዎችንና የግብርና ምርቶችን አውድመዋል፤ ዘርፈዋል ፤በርካታ ዜጎችን ገለዋል ፤አቁስለዋል፤ አፈናቅለዋል። ይህ ሁኔታ ደግሞ ከአለም አቀፍ ህግ ጋር የሚጣረስ እንደ ወዳጅ አገርም የማይጠበቅ በመሆኑ አሁንም ችግሩን በሰላማዊና በተረጋጋ መንፈስ መመልክት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል። የኢትዮጵያና የሱዳን ህዝቦች ረጅም ዘመንን ያስቆጠረ የታሪክ የባህል እንዲሁም የንግድ ግንኙነት ያላቸው ናቸው።፣ በድንበር ላይ የተፈጠረውና ዓለም አቀፍ ህግን በተቃረነ መልኩ በሱዳን ወታደሮች የተፈጸመው አሳዛኝ ድርጊት ሊታረም ጉዳዩም በድርድር ሊፈታ የሚገባው መሆኑን ገልጸዋል። ይህንንም ለማድረግ የሚያስችሉ መዋቅሮች መዘርጋታቸውን ጠቁመው፣ የሱዳን ጦር በህገ ወጥ መንገድ የያዘውን አካባቢ ለቆ መውጣት እንዳለበትም አስታውቀዋል። ግጭት ውስጥ መግባት ለሁለቱም አገሮች አይጠቅምም። የሁለቱን አገሮች ዝቅታ የሚፈልገውና ከዚያም የሚጠቀመው ሶስተኛ ወገን አለመግባባቱ ወደግጭት እንዲያመራ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑን የሁለቱም አገራት ህዝቦች ያውቃሉ ያሉት አምባሳደር ኢብራሂም፤ ችግሩ ከዘላቂ ጥቅማቸውና ግንኙነታቸው በታች መሆኑን በመረዳት የድንበር አለመግባባቱን በሰከነና በሰላማዊ መንገድ መፍታት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። የኢትዮ ሱዳን የድንበር ኮሚሽን አባል አቶ ወሂብ ሙሉነህ በበኩላቸው፣ ማንኛውም የድንበር ጉዳይ በድርድር ሊፈታ የሚገባው ፤ ወደ ጦርነት መግባት ግንኙነታቸው ላይ ከፍተኛ የሆነ አደጋን ይፈጥራል ብለዋል።እንደ አቶ ወሂብ ገለጻ ፣ ሁለቱ አገሮች የገጠማቸው ችግር ሊፈጠር የሚችልና በተለይም ደግሞ እንደነሱ አይነት በባህል በንግድ እንዲሁም በህዝቦች መስተጋብር አብሮ የቆየን ማህበረሰብ ግንኙነት ሊያሻክር የማይችልና የማይገባ መሆኑን በመረዳት ችግሩን በሰከነ መንገድ በሰላማዊ ሁኔታ ለመፍታት መጣር፣ የተዘረጉ መዋቅሮችንም መጠቀም እንደሚገባ አስረድተዋል። አካባቢው ላይ ብዙ ዓይነት ጂኦግራፊካል ስራዎች በተለያዩ ጊዜያት ተሰርተዋል ያሉት አቶ ወሂብ፤ እነዚህን ስራዎች ወደ መሬት አውርዶ የጋራ ቴክኒካል ኮሚቴ አቋቁሞና በገለልተኛ ቡድን እንዲጣራ አድርጎ ችግሩን መፍታት ሌላው አማራጭ እንደሆነ አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ\n29/2013 ", "passage_id": "b432bb6c8ce4a2226fc31d0bf41d41c3" }, { "passage": " “ግብጽ በደቡብ ሱዳን ወታደሮችን እያሰለጠነች ነው” የሚሉ ዘገባዎች ባለፉት ሳምንታት ወጥተው እንደነበር ይታወሳል፡፡ ዘገባዎቹ በዋናት ሲሰራጩ የነበረው በአልጄዚራና በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ነበር፡፡ ከዚህ ባለፈም ደቡብ ሱዳን ለግብጽ የወታደር ማሰልጠኛ ቦታ ፈቀደች የሚሉና ሌሎችም ጁባን ፣ አዲስ አበባንና ካይሮን የሚመለከቱ ዘገባዎች መውጣታቸው ይታወሳል፡፡\nይህንን ተከትሎ በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ኤምባሲ ደቡብ ሱዳን ምንም አይነት የወታደር ማሰልጠኛ ቦታን ለግብጽም ሆነ ለየትኛውም ሀገር አለመስጠቷን ዜናዎቹም ውሸት መሆናቸውን መግለጹ ይታወቃል፡፡ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም ጉዳዩ ፍጹም ከእውነት የራቀ ስለመሆኑ ገልጿል፡፡\nይህን ጉዳይ በተመለከተ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ምክትል አምባሳደር ዴቪድ ደንግ ኮንግ በደቡብ ሱዳን ውስጥ አንድም የግብጽ ወታደር አለመኖሩን እና ምንም አይነት መሬት ለየትኛውም ሀገር አለመሰጠቱን አረጋግጠዋል፡፡\nበደቡብ ሱዳን በኩል አድርጎ ኢትዮጵያን ሊጎዳ የሚችል የትኛውም ሃይል በሀገራቸው ተቀባይነት እንደሌለው ያነሱት አምባሳደር ዴቪድ ደንግ ኢትዮጵያ ጎረቤታችን ብቻ ሳትሆን ሁሉም ነገራችን ናት ብለዋል፡፡\n“ከኢትዮጵያ ጋር ድንበር ብቻ አይደለም የምንጋራው” ያሉት ዲፕሎማቱ “ህዝባችን ፣ ባህላችን ፣ ቋንቋችን እና ሌሎች ነገሮቻችንም የተያያዙና የተሳሰሩ ናቸው” ብለዋል፡፡ “በደቡብ ሱዳን በኩል ኢትዮጵያን እጎዳለሁ ብሎ ያሰበ ሃይል በቅድሚያ የሚጣላው ከደቡብ ሱዳን ጋር ነው” ሲሉም ምክትል አምባሳደሩ ለአል ዐይን ተናግረዋል፡፡\n“የትኛውም አካል ኢትዮጵያን በደቡብ ሱዳን በኩል ሊያጠቃ እንደማይችል የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማረጋገጡንም ነው የገለጹት፡፡\n“የተሳሳቱ መረጃዎችን በማሰራጨት የሰላም ጸር የሆኑ ሰዎች የሚነዙት ወሬ ብዥታን ሊፈጥር አይገባም” ብለዋል ምክትል አምባሳደሩ፡፡\nከሰሞኑ የሕዳሴ ግድብን ድርድር በሚመለከት ግብጽ ጉዳዩን ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት መውሰዷ አግባብ እንዳልሆነ የገለጹት የደቡብ ሱዳን ምክትል አምባሳደር ጉዳዩ በአፍሪካ ማለቅ ሲገባው ወደ ኒውዮርክ መውሰዱ ትክክል እንዳልሆነ አብራርተዋል፡፡\nአምባሳደር ዴቪድ ደንግ አዲስ አበባም ሆነ ካይሮ የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት መሆናቸውን አንስተው አፍሪካ ህብረትን አልፎ ወደ ተባበሩት መንግስታት መውሰድ አግባብ አይደለም ነው ያሉት፡፡\nኢትዮጵያና ግብጽን ያላስማማው ጉዳይ በአፍሪካ ደረጃ ሳይታይ ወደሌላ የዉጭ አካል መወሰዱ ተገቢነት የሌለውና የአፍሪካን ችግር በራስ አቅም ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት የሚጻረር መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡\n", "passage_id": "1458d0861628fe162f20532dc9a2eff6" }, { "passage": "የሱዳን ታጣቂዎችና ሚሊሻዎች ከሰሞኑ የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው ጥቃት መፈፀማቸውን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ፡፡ሚሊሻዎቹ  እና  ታጣቂዎቹ የገበሬዎችን ማሳ በመዝረፍ እና በማፈናቀል በርካታ ህገ ወጥ ድርጊት መፈጸማቸውን አምባሳደር ዲና ከዋልታ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ከሱዳን አመራሮች ጋር እየተነጋገረ መሆኑን የገለጹት አምባሳደር ዲና፣ በሀለቱ ሀገራት መካከል ልዩነትን ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላትና ወደ ሱዳን የሸሸው የጁንታው ቡድን ሁኔታው እንዲባባስ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡የመሬት ይዞታ ባለቤትነት ጥያቄ በአንዳንድ የሱዳን ፖለቲከኞችም ይስተዋላል ያሉት ቃልአቀባዩ፣ ድርጊቱን በመደገፍ በሱዳን የሚገኙ መገናኛ ብዙኃንም ሲያራግቡት መቆየታቸውን አንስዋል፡፡ከሰሞኑ በሱዳን በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይም ብሔርን መነሻ ያደረገ ማጎሳቆል እንደደረሰባቸውም ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያ በህግ ማስከበር ሂደት ውስጥ መሆኗን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የሀገሪቱን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩ አካላት ሁኔታዎችን ለማባባስ እየሰሩ መሆናቸውም ተነግሯል፡፡(በመስከረም ቸርነት)", "passage_id": "d79d49719874bace7683693ba12e7fad" }, { "passage": " በደቡብ ሱዳን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ፡፡የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በተለይ ለኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቭዥን ድርጅት በሰጡት ማብራሪያ ሰሞኑን ተሞክሮ የጨነገፈውን የደቡብ ሱዳን መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ በመዲናዋ ጁባና በሌሎች የሃገሪቱ  ግዛቶች ግጭት ተስፋፍቷል፤ ይሁን አንጂ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ እስከ አሁን ምንም አይነት ችግር እንዳልደረሰ ገልፀዋል፡፡በደቡብ ሱዳን የሚገኙ የኢትዮጵያ ዜጎችን ጁባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታታለ ነው ያሉት ቃል አቀባዩ፣ በሃገሪቷ አሁን ያለው አለመረጋጋት እየከፋ የሚሄድ ከሆነ ዜጎች ሳይጎዱ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ ይድረጋል ብልዋል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በደቡብ ሱዳን የሚገኙትን ኢትዮጵያውያንን  እንዳንጋገሯቸውና፣ በተረጋጋ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ መግለፃቸውን ቃል አቀባዩ ዲና ሙፍቲ አስረድተዋል፡፡የሰሞኑን የደቡብ ሱዳን  አለመረጋጋት  በዘላቂነት ለመፍታት የምስራቅ አፍሪካ የልማት  በየነ መንግስታት ኢጋድ ሚኒስትሮች ባሳለፍነው ሳምንት በጉዳዩ  ላይ ጁባ ድረስ በማቅናት መክርዋል፡፡በውይይታቸውም በወቅቱ የደቡብ ሱዳን የፖለቲካ ቀውስ ላይ ኢጋድ ሁለት ዋና ዋና ውሳኔዎችን አስተላፏል፡፡ የመጀመሪያው አሁን የተፈጠረው አለመረጋት  በአስቸኳይ እንዲፈታ የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ  ሁሉም ቁርሾ ያላቸው የፖለቲካ ወገኖች አለመግባባታቸውን በጠረጴዛ ዙርያ እንዲፈቱ መሰረት ያደረገ ምክረ ሀሳብ እንደሆነ አምባሳደር ዲና ተናግረዋል ፡፡ኢትዮጵያ የቀጠናው ተዕፅኖ ፈጠሪ፣ የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር፣ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ  እንዲሁም ሁለቱ ሱዳንን  በሚመለከት ከህዝበ ውሳኔው በፊትና በኋላ በማደራደር ከፍተኛ ጥረት ያደረገችና እያደረገች ያለች ሃገር ከመሆኗ አንፃር  የሰሞኑን በደቡብ ሱዳን የተፈጠረው አለመግባባት እልባት እንዲያገኝና ሁለቱ ወገኖችም ችግሮቻቸውን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ከፍተኛ ጥረት ታደርጋለች  ብለዋል፡፡ አምባሳደሩ የደቡብ ሱዳንን ብሎም የቀጠናውን ዘለቂ ሰላም ለማምጣት ካስፈለገ በቀጠናው የሚገኙ ሃገራት ዜጎችን ችግርና ድህነትን ማስወገድ በምትኩም ልማትን ማፋጠን አማራጭ  የሌለው መፍትሄ  ነው ብለዋል፡፡ደቡብ ሱዳን ያልተሳካውን የመንግስት ግልበጣ ሙከራ ተከትሎ የተፈጠረው አለመግባባት አስከ አሁን ያልረገበ ሲሆን  ይህንን ወቅታዊ የፖለቲካ አለመግባባትም  በእንጭጩ እንዲቀጭ ኢጋድ፣ አፍሪካ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታትና ሌሎች ዓለም  ዓቀፍ ተቋማት ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ እንቅሳቃሴ ላይ  ናቸው፡፡የደቡብ ሱዳን ግጭት ከሁለት ሳምንት በፊት ወታደራዊ የደንብ ልብስ በለበሱ ታጣቂዎች  የተቀሰቀሰ ሲሆን እስከ አሁን ድረስ በመቶች የሚቆጠሩ ንፁሃን  ዜጎች ለህልፈት ተዳርገዋል፤ በርካቶች ደግሞ ቀያቸውን ጥለው ወደ መጠለያ ለመግባት ተገደዋል፡፡", "passage_id": "dda17d271ebd2630cde7b2b0cdc4d4ea" } ]
ba3cebe9fde3900ca76e26c8f14b8e78
6516d6619bfd30ac4c1db2c467fffdda
ቢሮው 73 ከመቶ ያህል ሰብል መሰብሰቡን አስታወቀ
-127 ሚሊዮን ኩንታል ሰብል ለመሰብሰብ እቅድ ተይዟል አስናቀ ፀጋዬአዲስ አበባ፡- በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ73 ከመቶ በላይ የሚሆን ሰብል መሰብሰቡን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ። 127 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብም መታቀዱ ተገልጿል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን መንግስቴ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ የዘንድሮው የግብርና ምርት አሰባሰብ በጎርፍና መሬት መንሸራተት፣ አምበጣ፣ ኮቪድና ጦርነት የተፈተነ ቢሆንም 73 ከመቶ በላይ የሚሆነውን ምርት መሰብሰብ ተችሏል። እንደ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ገለፃ፤ በክልሉ የተከሰተው የአምበጣ መንጋ 900 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ላይ የነበረ ሰብል ቢያወድምም፤ አምበጣው የተከሰተበት አካባቢ እምብዛም ምርታማ ባለመሆኑ ተፅእኖው ያን ያህል የከፋ አልሆነም። በክልሉ ባጠቃላይ 4 ሚሊዮን 282 ሺ 517 ሄክታር መሬት በሰብል መሸፈኑን የተናገሩት ምክትል ቢሮው ኃላፊው፤ እስካሁን ድረስ 3 ሚሊዮን 112 ሺ 165 ሄክታር ሰብል መሰብሰቡን አስታውቀዋል። በዚህም ከ73 ከመቶ በላይ ሰብል መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመዋል። በዚሁ የሰብል አሰባሰብ ወቅት 115 የሚሆኑ ኮምባይነሮችን በመጠቀም 847 ሺ 515 ኩንታል ስንዴ ለመውቃት መቻሉንም ገልፀዋል። ይህም 23 ሺ 30 ሄክታር የሚጠጋ መሬት እንደሆነና ከባለፈው ዓመት ጋር ሲወዳደር የተሻለ አፈፃፀም እንደሆነም ምክትል ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል። በግዳጅ ላይ ያሉ የአማራ ክልል ሚሊሻ አባላትን በማሳተፍ ሰብል እንዲሰበሰብ መደረጉንም ያነሱት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ሊመጣ ስለሚችል በከፍተኛ ርብርብ ሰብል የማሰባሰብ ተግባሩ እየተከናወነ እንደሚገኝም አመልክተዋል። በዚህ ዓመት ባጠቃላይ ወደ 127 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ እንደታቀደና በዓመቱ የታየው መልካም የዝናብ መጠንና ስርጭት የዘንድሮውን የምርት አሰባሰብ የተሻለ እንደሚያደርገውም ጠቅሰዋል። ያጋጠሙ ችግሮች እንዳሉ ሆነው የሰብል አሰባሰቡ አምና ከነበረው ጋር ሲነፃፀር መልካም የሚባል መሆኑንም ምክትል ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል። የሰብል አሰባሰብ አጠቃላይ አፈፃፀም የምርት ግምገማ ከተካሄደ በኋላ የሚታወቅ መሆኑንም ምክትል ቢሮ ኃላፊው ጠቁመው፤ ቀሪ 27 ከመቶ የሚሆነውና በደጋማው የክልሉ ክፍሎች የሚገኘው ያልተሰበሰበ ሰብል እንደደረሰ በቀጣይ እንደሚሰበሰብም ጠቅሰዋል። በምርት አሰባሰብ ወቅት ብክነት እንዳያጋጥም እንደተለመደው ኮምባይነሮችንና ሌሎችንም የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርት እየተሰበሰበ መሆኑንም ምክትል ቢሮ ኃላፊው አያይዘው ገልፀዋል። በጥቅሉ የክልሉ የዘንድሮው የሰብል አሰባሰብ ያለበት ደረጃ መልካም የሚባል መሆኑንም አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37698
[ { "passage": "በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከተለያዩ የገቢ ምንጮች 690 ሚሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ ከዕቅዱ በላይ ማሳካቱን የክልሉ ገቢዎች ኤጄንሲ አስታወቀ፡፡የኤጄንሲው ኃላፊ አቶ ኢብራሂም መሃመድ  እንደገለፁት፤ የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ100 ሚሊዮን ብር ጭማሪ አለው ፡፡ይሁንና የተሰበሰበው ገቢ ክልሉ ካለው የገቢ አማራጭ አንጻር ሲታይ አነስተኛ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ይህም በወረዳዎች የገቢ አሰባሰብ አደረጃጀት ባለመኖሩ ስራው እንደተጨማሪ ስራ መታየቱና ከፍተኛ የአመራር ቁርጠኝነት ማነስ ገቢው በአግባቡ እንዳይታቀድና እንዳይሰበሰቡ ማነቆ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ይህን ችግር ለመፍታት ኤጀንሲው በአዲሱ የበጀት ዓመት በ32ቱም ወረዳዎች የቁርጥ ግብር ጥናት ለማካሄድ ማቀዱን ገልጸዋል ፡፡በአፋር ክልል በአዲሱ የበጀት ዓመት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ግብር  ለመሰብሰብ በትኩረት እንደሚሰራ ነው ያስገነዘቡት፡፡(ኢዜአ)", "passage_id": "1f1c679696488ee0415d07251685b0bb" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 12/2005 (ዋኢማ) – በመኸር እርሻ የተሻሻለ የአዘራር ዘዴን በመተግበርና የምርት ግብዓትን በስፋት በጠቀም ረገድ ከፍተኛ ለውጥና አበረታች ውጤት መታየቱን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸል። የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን በኦሮሚያ ክልል በአርሲና ምስራቅ ሸዋ ዞኖች የተለያዩ ወረዳዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ወቅቱ በግብርናው ዘርፍ የዘር ሥራ የሚሰራበት ዋነኛው የተግባር ምዕራፍ ነው። በመሆኑም በምርት ዘመኑ የግብርናን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ከዝግጅት ሥራው ጀምሮ በተለይ በዚህ ዓመት በተለየና ጠንከር ባለ ሁኔታ ለመስራት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። ከሚሰራው የዝግጅት ሥራ በዋናነት በአመራሩ፣ በፈፃሚው፣ በአርሶ አደሩና በየደረጃው ባሉና ከአሁን በፊት የታዩ የአመለካከትና የክህሎት እንዲሁም በግብዓት አቅርቦት፣ በአሰራር፣ በአደረጃጀትና በክትትልና ድጋፍ ጉድለቶች ላይ እስከ አርሶ አደሩ መንደር የሚዘልቅ ሰፊ ስልጠና መስጠት ያካተተ መሆኑን አመልክተዋል። ህም የአርሶ አደሮችን የአንድ ለአምስት፣ የልማት ቡድንና የጎጥ አደረጃጀቶችን በመጠቀም በአመለካከትና በክህሎት ስልጠናዎች አቅም በመገንባት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ሰፊ ሥራ የተሰራበት የምርት ዘመን ነው ብለዋል። ወደ ቀጣዩ ተግባር በመግባትም አርሶ አደሩ የዘር ሥራ ከመጀመሩ በፊት የማዳበሪያ አቅርቦት በየአካባቢው ቀድሞ እንዲደርስለት የማድረግ ሥራ በበቂ መጠን ተሰርቷል። በተመሳሳይም አስተማማኝ የምርጥ ዘር አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል በፌዴራል የምርጥ ዘር አባዢ ተቋምና በክልሎች እንዲሁም በግል ባለኃብቶች የሚባዛው ዘር ጥራቱ የተረጋገጠ እንዲሆንና በወቅቱ እንዲደርሱ ለማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ መደረጉን አመልክተዋል።አርሶ አደሩ በዘር ቅድመ ማስፋት የተሰጡትንና አዳዲስ ዝርያዎች ወደ አካባቢው እንዲገቡና እንዲላመዱ በማድረግ ጥራቱ ተጠብቆ በአንድ ለአምስትና በሌሎች የልማት ቡድን አደረጃጀቶች አማካኝነት ምርጥ ዘር ያያዙት ለሌላቸው እንዲለዋወጡ በማድረግ የምርጥ ዘር ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ሥራ ተሰርቷል፡፡ በዚህ ረገድ በዚህ ዓመት ሰፊ የሆነ መሻሻል መታየቱን የጠቀሱት ሚኒስትሩ በአንዳንድ አካባቢዎች ስነ-ምህዳሩ ለዘር ጊዜ ዘግየት ይላል በሚል መዘናጋት የዘገዩ አካባቢዎች መኖራቸውን በመለየት የተፋጠነ እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲገቡ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላው ምርታማነትን ለማሳደግ በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ ሰብሎችን በመስመር መዝራት ላት ትኩረት የተደረገ ሲሆን ይህም ሰብሉ በእጽዋት ምግብ መሻማት ምክንያት ምርታማነቱ እንዳይቀንስ የሚያደርግ መሆኑን አቶ ተፈራ ገልጸዋል። የአረምና የተባይ መከላከል ሥራ በቀላሉ ለመስራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተመቸ በመሆኑም አርሶ አደሩ በስፋት በስልጠና ያገኘውን ግብዓት በመጠቀም መሬት ላይ እንዲሰራው ለማድረግ ጥረት መደረጉንም ጠቁመዋል፡፡ በዚህ ረገድ ቀድመው ከሚዘሩ የበቆሎና ማሽላ ሰብሎች ጀምሮ በመስመር የመዝራት ስራው በዚህ ዓመት ባለፉት ዓመታት ከነበረው ከእጥፍ በላይ መሻሻል የታየ ሲሆን አሁን ባለበት ሁኔታ ደግሞ ቀሪዎቹም ሰብሎች በዚሁ ዘዴ በስፋት እንዲሰሩ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ የስንዴና የጤፍ ሰብሎች በመስመር የመዝራት ሁኔታ ካሁን በፊት በስፋት ያልተኬደበትና እንደነበር ሚኒስትሩ እሰታውሰው በዚህ ዓመት በመስክ ጉብኝቱ በተጨባጭ እንደታየው በተለይ በአርሲ ዞን በሚገኙ ወረዳዎች 85 በመቶ የሚሆነው የስንዴ ማሳ በመስመር መዘራቱን ገልጸዋል፡፡ በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜና አድአ ወረዳዎች እንደታየው ደግሞ ጤፍ በስፋት በመስመር እየተዘራ ሲሆን ሌሎችም ይህንኑ ተከትለው እንዲሰሩ ለማድረግ በተግባር ምዕራፉ ውስጥ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። በቀጣይ እስካሁን የተሰራውን ሥራ ይዞ በቀሪዎቹ የዘር ጊዜያት ሁሉም አርሶ አደር በዚሁ መንገድ እንዲሰራ ማድረግ በጥልቀት መሰራት ያለበት መሆኑን አሳስበዋል። በዚህ ዓመት በአርሶ አደሩ ዘንድ ያለው ማዳበሪያ የመጠቀም ሁኔታ ከፍተኛ መሻሻል ቢታይም በተሻለ ሁኔታ በመስመር የዘሩ አካባቢዎች የቴክኖሎጂ ጥንቅሩን የተሟላ አድርጎ በመፈጸም ረገድ የተጓደለ ነገር መታየቱን ጠቁመዋል። በቀጣይ እስካሁን የተሰራውን ሥራ ይዞ በቀሪዎቹ የዘር ጊዜያት ሁሉም አርሶ አደሮች በዚሁ መንገድ እንዲሰሩ ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል። በአጠቃላይ ምርታማነትን ለማሳደግ ተቀናጅተውና ተዋህደው መሰራት ያለባቸው የግብርና ልማት ተግባራትና የፓኬጁ ጥንቅር አካላት በተሟላ መንገድ እንዲፈጸሙ ለማድረግ ከስልጠና ጀምሮ በግብዓት አቅርቦትና የተሻሻሉ የአሰራር ዘዴዎችን በመተግበር በኩል የታየው መሻሻል እቅዱ በትክክለኛው አቅጣጫ ላይ እየሄደ መሆኑን ያሳየ ነው ብለዋል። እየታየ ያለው እንቅስቃሴ ተስፋ የሚሰጥና የተቀመጠውን የ20 በመቶ እድገት ለማረጋገጥ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ እንደሆነ የሚያሳይ ነው ያሉት አቶ ተፈራ አጠቃላይ ውጤቱ በቀሪዎቹና ባልተጠናቀቁ ስራዎች ላይ የሚመሰረት እንደሆነም አብራርተዋል። ይህን ውጤት በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥም መከናወን ያለባቸው የአረም፣ የተባይ መከላከል፣ ምርቱን በወቅቱ የመሰብሰብና ሌሎች ተግባራት ትኩረት በመስጠት አጠናከሮ መቀጠል እንደሚገባም አመልክተዋል። እንደ ኢዜአ ዘገባ በእስካሁኑ እንቅስቃሴ በየደረጃው ያለው የአመራር፣ የልማት ጣቢያ ሰራተኞችና ሙያተኞች አርሶ አደሩ ማሳ ድረስ ወርደው የመደገፍ ተግባር ከመቼውም ጊዜ በላይ የተሻለ ቢሆንም ክትትልና ድጋፉ ሰብሉ እስከሚሰበሰብበት ወቅት ድረስ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል፡፡", "passage_id": "3e4300a0c94f740e5818ac6e9be1ff10" }, { "passage": " አዲስ አበባ፡- በተያዘው የምርት ዘመን ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ በከፍተኛ ርብርብ ከተዘራ ሰብል ውስጥ 60 በመቶ የሚሆነውን ምርት መሰብሰብ መቻሉን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ \n የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሳኒ ረዲ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት መረጃ፤ በምርት ዘመኑ \nበመኸር በአገር አቀፍ ደረጃ 13 ነጥብ 55 ሚሊዮን ሄክታር በማልማት 382 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ \n13 ነጥብ 51 ሄክታር በዘር መሸፈን ተችሏል፡፡ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በተዘራው ሰብል ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ በተደረገው ርብርብ በአጠቃላይ 8 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር ወይም 60 በመቶ ያህል መሰብሰብ ተችሏል፡፡ የመኸር ሰብል በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች እየተሰበሰበ ሲሆን፤ በአማራ ክልል 61 ነጥብ 2 በመቶ፣ በኦሮሚያ ክልል 52 ነጥብ 5 በመቶ፣ በትግራይ ክልል 81 በመቶ፣ በደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል 55 ነጥብ 6 በመቶ በቤንሻንጉል ክልል 24%፣ በሐረሪ ክልል 92 እንዲሁም በጋምቤላ ክልል መቶ በመቶ ተሰብስቧል፡፡ \nከብሄራዊ ሜትዎሮሎጂ ኤጀንሲ ያገኘው መረጃ፤ የታህሳስ ወር የአየር ጠባይ ቅድመ ትንበያ በአዛኛው አካባቢ ደረቅ፣ \nፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ጠባይ እንደሚያመዝን ቢሆንም፤ በተከሰተው የአየር ለውጥ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ \nእንደተከሰተ ነው ግብርና ሚኒስቴር የገለጸው፡፡ በኦሮሚያም ክልል ምዕራብ እና ምሥራቅ ወለጋ፣ ጅማ፣ \nኢሉአባቦራ፣ አርሲ እና ባሌ፣ ምዕራብና ምሥራቅ ሐረርጌ፣ የጉጂ እና የቦረና ዞኖች፤ ጋምቤላ፣ አዲስ አበባ፣ \nአብዛኛው የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል፤ ከአማራ ክልል ምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ የደቡብ እና የሰሜን \nወሎ ዞኖች ፣ ሰሜን ሸዋ፤ የደቡብ ትግራይ ዞን፣ በሶማሌ ክልል የሚገኙት አብዛኛዎቹ ዞኖች በአብዛኛው መደበኛውና \nከመደበኛ በላይ ዝናብ ያገኛሉ፡፡ አዲስ ዘመን ቅዳሜ ታህሳስ 4/2012 ዋለልኝ አየለ", "passage_id": "0c4c6cf46a172fe08f2a5bbfeede3144" }, { "passage": "በአማራና ትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የአንበጣ መንጋ ተከስቷል፤ ጉዳት ሳያደርስ ለመከላከልም እየተሠራ ነው፡፡የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ሰሎሞን አሰፋ (ዶክተር) ለአብመድ እንደገለጹት በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ ደቡብና ሰሜን ወሎ ዞኖች የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተውን የአንበጣ መንጋ ለመከላከል በልዩ ትኩረት እየተሠራ ነው፡፡ በራያ ቆቦ፣ ሀብሩ፣ ጂሌ ጥሙጋ፣ ባቲና አርጎባ ልዩ ወረዳ አካባቢዎች የተለያዬ መጠን ያለው የአንበጣ መንጋ ተከስቷል፤ ለመቆጣጠርም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ዶክተር ሰሎሞን እንዳመለከቱት በባሕላዊና ዘመናዊ መንገድ የአንበጣ መንጋውን ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ‹‹እስካሁን በሰብልም ሆነ በግጦሽ ሳር ላይ ጉዳት አላደረሰም›› ያሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው አስፈላጊው የበጀትና የኬሚካል ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ የአንበጣ መንጋው ተረጋግቶ አንድ አካባቢ ላይ ከሠፈረ በአውሮፕላን ኬሚካል ለመርጨት ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት ክትትል እየተደረገ እንደሆነም አመልክተዋል፡፡", "passage_id": "fcc583a825c6348d3765b59500ec325e" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በመጤ ተምች ተወሮ ከነበረው የበቆሎና ማሽላ ሰብል ከተዘራ ማሳ ውስጥ 51 ሺህ ሄክታሩ ኬሚካል በመርጨትና በባህላዊ ዘዴ መከላከል መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።\nየቢሮው የሰብል ጥበቃ ባለሙያ አቶ አሻግሬ እንዳየን የአሜሪካ መጤ ተምች ካለፈው ሰኔ አጋማሽ ጀምሮ በ57 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በለማ የበቆሎና ማሽላ ሰብል ተከስቶ መቆየቱን አስታውሰዋል።\nየተከሰተውን አውዳሚ ተምችም የሰው ጉልበትን በመጠቀም በባህላዊ መንገድ እና ኬሚካል በመርጨት በሰብል ላይ ጉዳት ሳይደርስ ማስወገድ መቻሉን ተናግረዋል።\nበመከላከል ስራው ከ16 ሺህ ሊትር በላይ ፀረ-ተባይ ኬሚካል ጥቅም ላይ ሲውል ከ114 ሺህ የሚበልጡ አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች መሳተፋቸውንም ገልፀዋል።\nበቀሪ ስድስት ሺህ ሄክታር መሬት የሚገኘውን የአሜሪካ መጤ ተምች በሰብል ላይ የከፋ ጉዳት ከማድረሱ በፊት የማስወገድ ስራም በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።", "passage_id": "fe99806c32e36efe98f56056559f5e06" } ]
8277b84eb86f6dd23d0c1806e912d27d
203338a01e78370146af50b0a92b5a2f
ሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በአምስት የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን 424 ተማሪዎች አስመረቀ
ዳንኤል ዘነበ አዲስ አበባ ፦ሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በአምስት የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪና እና በድህረ ምረቃ መርሐ ግብር ያስለጠናቸውን 424 ተማሪዎችን ትናንት አስመረቀ። በዕለቱ የተመረቁት ተማሪዎች በ2012 ዓ.ም መመረቅ የነበረባቸው እና በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት በመቋረጡ ምክንያት የተላለፈ መሆኑም ታውቋል፡፡የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ፕሬዚዳንት ዶክተር ተረፈ ፈየራ በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት፤ የመማር ማስተማር ሂደቱ በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ምክንያት ቢቋረጥም፤ ተማሪዎቹ የማካካሻ ትምህርት ወስደው ለምርቃት በቅተዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ በአምስት የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ እና በድህረ ምረቃ መርሐ ግብር ሲያስተምራቸው የነበሩ 424 ተማሪዎችን አስመርቋል ብለዋል።ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ካስመረቃቸው አጠቃላይ ተማሪዎቹ 368 በመጀመሪያ ዲግሪ፤ 44ቱ ደግሞ በድህረ ምረቃ መርሐ ግብር በቀንና በማታው የትምህርት መርሐ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ መሆናቸውን ገልፀዋል። በመጀመሪያ ዲግሪ ለሰባት ተከታታይ ጊዜያት በሁለተኛ ዲግሪ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ ማስመረቁን ተናግረዋል።«ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ የትምህርት ፍላጎትና አቅም እያላቸው ከፍለው መማር የማይችሉ ችግረኛ ወጣቶችንም የከፍተኛ ትምህርት ዕድል ይሰጣል» የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ወጣቶቹ ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን መርዳት እንዲችሉ ብሎም በሀገር ግንባታ ላይ አዎንታዊ ሚና እንዲኖራቸው የራሱን ድርሻ በማበርከት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።ተቋሙ በየዓመቱ ከ200 ተማሪዎች በላይ የነፃ የትምህርት እድል ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን በመጠቆምም፤ በዚሁ መሰረት በዲግሪ መርሐ ግብር ተመራቂ ከሆኑት 368 ተማሪዎች 58 በነፃ እድል ተጠቃሚ የነበሩ መሆኑን አብራርተዋል። ሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ባለፉት ሰባት ዓመታት በመጀመሪያ ዲግሪ 1ሺህ488 ተማሪዎች፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ደግሞ 44 ተማሪዎችን በድህረ ምረቃ፤ በአጠቃላይ 1ሺህ532 ተማሪዎችን ያስመረቀ መሆኑ ታውቋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37703
[ { "passage": "አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዚህ አመት ከ9 ሺህ 600 በላይ ተማሪዎችን የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 30 ቀን 2010 ዓ ም እንደሚያስመርቅ ገለፀ።የዩኒቨርሲቲው ምክትል ሬጅስትራር አቶ መሰለ ብርሃኑ እንደገለፁት፤ በመደበኛ፣ በማታ፣ በርቀትና በክረምት መርሃ ግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎችን የክብር እንግዶች በሚገኙበት ነው የሚያስመርቀው።ከተመራቂዎቹ መካከል 2 ሺህ 734 ሴቶች ናቸው።ከአጠቃላይ ተመራቂዎቹ  5 ሺህ 972 በቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር የተማሩ ሲሆኑ 3 ሺህ 606 ደግሞ በድህረ ምረቃ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን የተከታተሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።266ቱ በሶስተኛ ዲግሪ የሚመረቁ መሆናቸውንም ገልፀዋል።የወርቅ ሜዳሊያ ከሚሸለሙ 12 ተመራቂዎች መካከል ሰባቱ ሴቶች እንደሆኑ የጠቆሙት አቶ መሰለ ውጤቱ በዩኒቨርሲቲው ለሴቶች የሚደረገውን ድጋፍና ተሳትፎ የሚያሳይ እንደሆነ ተናግረዋል።ለተመራቂዎችና ቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕታቸውን ያስተላለፉ ምክትል ሬጂስትራሩ ተመራቂዎች በስራ መስክ ላይ ውጤታማ እንዲሆኑ ተመኝተዋል።ዘንድሮ ዩኒቨርሲቲው የክብር ዶክትሬት ማዕረግ የማይሰጥ መሆኑን ከሬጅስትራሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።(ኢዜአ)", "passage_id": "5303809eca8c5924e23e86057e69c7fe" }, { "passage": "ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ አዲስ አበባ፣ አሜሪካ ከሚገኘው ሊንከን ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ለ6ኛ ጊዜ በማስተርስ ኦፍ ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን (ኤም ቢ ኤ) እና በመጀመሪያ ዲግሪ (ቢኤ) ፕሮግራም ለመጀመሪያ፣ ያስተማራቸውን ተማሪዎች ነገ በኢሲኤ አዳራሽ ያስመርቃል፡፡ ዌስተርን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ፣ ከሊንከን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር፣ ላለፉት አምስት ተከታታይ ዙሮች በማስተርስ ኦፍ ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን (ኤምቢኤ) 143 ተማሪዎችን በጥራት አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን ነገ ደግሞ 27 ተማሪዎችን በኤምቢ ኤ፣ 18 ተማሪዎችን በቢዝነስ አስተዳደር (ቢኤ) በመጀመሪያ ዲግሪ እንደሚያስመርቅ ታውቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በሚቀጥለው ዓመት በዳይኖስቲክ ኢሜጂንግ በድግሪ መርሃ ግብር ሥልጠና ለመጀመሪያ በዝግጅት ላይ መሆኑን የተቋሙ ፕሬዚዳንት አቶ አቤቱ መላኩ የገለፀ ሲሆን፣ በጥራት ላይ ተመስርቶ ብቃት ያላቸው ዜጎች ኮትኩቶ ማሳደግ አስፈላጊ በመሆኑ ከመዋለ ህፃናት ጀምሮ እስከ ድህረ ምረቃ የሚደርስ የትምህርት መርሐ ግብር ለመዘርጋት ማቀዱን ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "ceaf886f66e33c6a4e491ce34e1a993d" }, { "passage": "አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ  87 የሕክምና ዶክተሮችን ዛሬ ሲያስመርቅ ከተመራቂዎች ውስጥ 32ቱ ሴቶች ናቸው፡፡በምረቃ ስነስርአቱ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ዳምጠው ዳርዛ ዩኒቨርሲቲው የሕክምና ዶክተሮችን ማሰልጠን የጀመረው በዘርፉ ያለውን የባለሙያ እጥረት ለመቅረፍ መሆኑንም አስታውሰዋል፡፡የእለቱ የክብር እንግዳ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ ተመራቂዎች ከፊታቸው የተመራቂዎቹን  አገልግሎት የሚጠብቁ ዜጎች እንዳሉ በመገንዘብ ሙያዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ከወዲሁ ሊዘጋጁ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡በ2001 ዓ.ም የሕክምና ዶክተሮችን ማሰልጠን የጀመረው ዩኒቨርሲቲው የዛሬውን ጨምሮ ለ7ኛ ጊዜ  ያስመረቀ ሲሆን እስካሁን 572 የሕክምና ዶክተሮችን ማስመረቁም ተገልጿል፡፡(በአለበል አለማየሁ)", "passage_id": "7efa57bf739e3cb6297e54955362eda2" }, { "passage": "1ሺህ 266 ተማሪዎች ዛሬ አስመረቀ።ዛሬ የተመረቁት ተማሪዎች በግብርናና ተፈጥሮ ሀብት፣ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ፣ በጤና ሳይንስ ኮሌጆች የሰለጠኑ መሆናቸው ታውቋል።ከተመራቂዎቹ መካከል 555 ሴቶች እና 711 ወንዶች መሆናቸው ተገልጿል፡፡በምረቃ በሥነ-ሥርዓቱ የፌዴራልና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!", "passage_id": "edb9aefdd6978d2caf2de013c8da3119" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ33ኛ ዙር በተለያዩ ሙያዎች ያሰለጠናቸውን ከ2 ሺህ 300 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡ዩኒቨርሲቲው በድህረ ምረቃና በቅድመ መደበኛ መረሃ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ነው ያስመረቀው፡፡ተመራቂዎች የሀገሪቱ ብሎም የዓለም የጤና ስጋት ከሆነው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለትህምርት የማይመች ሁኔታን ፈጥሮ ቢሆንም ጥንቃቄ በማድረግና በቴክኖሎጂ በመጠቀም የትምህርት እና የምርምር ሥራቸው ሳይቋረጥ መጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ ተናግረዋል ፡፡ተቋሙ በልዩ ልዩ የምህንድስና፡ የህክምና፡ የጤና፡ የግብርና፡ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ እና በሌሎች የማህበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፎች እስከ አሁን የዛሬዎችን ጨምሮ አጠቃላይ 56 ሺህ 958 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡በተመሳሳይ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 43 ተማሪዎችን ዛሬ አስመረቋል።ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያና ሁለተኛ ድግሪ ያስተማራቸውን ተማሪዎች ሲሆን ያስመረቀው በኪቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተማሪዎቹ የቀሯቸውን ትምህርቶች በኦንላይን ተከታትለው\nመጨረሳቸው በምረቃው ላይ ተገልጿል።የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ጫና ዋታ በስነ ስርዓቱ ላይ ለተማሪዎቹ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስትላልፈዋል።\nተማሪዎቹ ከኮሮናቫይረስ ራሳቸውን በመጠበቅ ሀገራቸውን እና ህዝባቸውን የሚጠቅም ስራ እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል።ፕሬዚዳንቱ በአሁኑ ወቅት ዩኒቨርሲቲው 17 ሺህ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት መርሃ ግብሮች ተቀብሎ እያስተማረ ቢሆንም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ግን የመማር ማስተማር መርሃ ግብሩ ተቋርጦ እንደሚገኝ አብረው ጠቁመዋል።በአስጨናቂ ጉዱና አዳነች አበበ", "passage_id": "1e1c51e1361d4e82c1f68cc4e663f981" } ]
d7d9775aa01fb9910228fde827446019
75c7c4e7bf9cf5db1cb3240497f4ccf6
ተመራቂዎች ቴክኖሎጂን በማህበረሰቡ ውስጥ ለማስረጽ መስራት እንዳለባቸው ተገለጸ
ፋንታነሽ ክንዴአዲስ አበባ፡- የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሚወጡ ተመራቂዎች ሳይንስ በማህበረሰቡ ውስጥ ባህል ሆኖ እንዲሰርጽ መስራት እንዳለባቸው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ገለፁ፡፡ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትናንት ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት ፕሮፌሰር አፈወርቅ፣ ለተመራቂ ተማሪዎችና ለወላጆቻቸው እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፤ “ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያካበቱትን እውቀትና ክህሎት ከፍ ላለ ውጤት ለማዋል መዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል” ሲሉ አሳስበዋል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ገለጻ፤ ሳንይንስና ቴክኖሎጂ የአንድ አገር ሁለንተናዊ እድገት መሰረት ነው፡፡ ሳይንስ የኅብረተሰባችንን ሁለንተናዊ እድገት እንዲደግፍና የዕለት ከዕለት ህይወታቸው አካልና ባህል እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ የሳይንስ ባህል ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል፡፡ ተመራቂዎችም ሳይንስ ባህል ሆኖ ወደ ማህበረሰባችን በመስራት እንዲሰርጽ ሊደግፉንና ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡በእውቀትና በክህሎት ያደገ ማህበረሰብ ቴክኖሎጂ የመፍጠርና የመጠቀም አቅሙ ያድጋል፤ ህግና ስርዓት የሚያከብርና የአካባቢውን ችግር የሚፈታ ሀሳብ ያመነጫል፤ ያሉት ፕሮፌሰር አፈወርቅ፤ ከዚህ አኳያ አገራችን አሁን ካለችበት ዘርፈ ብዙ ችግር እንድትወጣና ከፊት ለፊቷ ያሉትን በርካታ ተስፋዎች እንድትጠቀም ለማስቻል ተመራቂዎች መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ለሚ ጉታ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር በማድረግ ረገድ ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን ኃላፊነት እየተወጣ ሲሆን፤ ለዚህ የሚሆን በሳይንስና ቴክኖሎጂ የሰለጠነ አቅም ያለው የሰው ኃይል እያፈራ ይገኛል፡፡ በዩኒቨርሲቲው መምህራን የምርምር ሥራዎችም እያደጉ በመምጣታቸው በአገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ ጭምር በኢንዱስትሪ-ዩኒቨርሲቲ ትስስሩ ትልቅ ሚና እየተወጣ ይገኛል፡፡በምርምርና ልህቀት ማዕከላቱ አማካኝነትም በህዋ ሳይንስ ላይ የበኩሉን ለመወጣት እየሰራ ሲሆን፤ ከዚህ በተጓዳኝ ለህብረተሰቡም ሙያዊ ድጋፍ እየሰጠ ይገኛል፡፡ በቀጣይም በርካታ ግዙፍ የምርምር ፕሮጀክቶችን እየሰራ ሲሆን፤ ኮሮናን በመዋጋት ጭምር ሲወጣ የነበረው ጠንካራ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ዶክተር ለሚ ያረጋገጡት፡፡ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ቆይታቸው ላሳዩት መልካምና ዓርአያነት ላለው ስነምግባር በማመስገን ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው እንኳን ደስያላችሁ ያሉት ዶክተር ለሚ፤ ለተመራቂ ተማሪዎች “አገሪቱን ወደፊት የሚያራምዱ ተግባራትን ማከናወን እንዲሁም የህዝቡን ኑሮ የማሻሻልና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት ከእናንተ ይጠበቃል እና የመማራችሁን ትርጉም በመገንዘብ ይሄንኑ በታላቅ ትጋትና ሥነምግባር እንድትፈጽሙ አደራ እላለሁ” ሲሉ አሳስበዋል፡፡ መጪው ዘመን በተሰማራችሁበት የስራ መስክ መልካም ውጤት የምታመጡበት እና ህዝባችሁን በቀናነት የምታገለግሉበት፣ አገራችሁንም ወደ ብልጽግና የምታሸጋግሩበት ዘመን ይሁንላችሁ፤ ሲሉም መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል፡፡ዩኒቨርሲቲው ትናትን 1ሺህ240 ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ በተለያየ መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ያስመረቀ ሲሆን፤ ከተመራቂዎች ውስጥ 1ሺህ 228 በመጀመሪያ ዲግሪ፤ 2 ደግሞ በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቁ ናቸው፡፡ በዕለቱ ከተመረቁት ውስጥም 274 ሴት ተመራቂዎች መሆናቸው ተገልጿል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37704
[ { "passage": "አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 07/2005 (ዋኢማ) – ፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ70/30 የመስኮች ቀመር የሚሰጡት ሥልጠና ተመራቂዎች ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስትሩ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደሳለኝ ሳሙኤል ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ተቋማቱ ከአገሪቱ የሰው ኃይል ፍላጎትን በመንተራስ የሚሰጡት ሥልጠና መጀመራቸው ፈጣኑን ማህበራዊና ዕድገት ዘላቂና በዕውቀት ላይ በተመሰረተ መንገድ ለማካሄድ ያስችላል፡፡ የተቋማቱ የማስመረቅ አቅም ከዓመት ወደ ዓመት እያደገ በመምጣቱ ዘንድሮ ከ70 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ማስመረቃቸው ከመነሻው ዝቅተኛነት አንፃር ሲታይ ከፍተኛ እድገትና ለውጥ እየታየበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ ሆኖም አገሪቱ ከሚያስፈልጋት በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ ባለሙያ፣ተመራማሪ፣አዲስ ዕውቀት አፍላቂና ሥራ መሪ ቁጥር አንፃር ሲታይ አሁንም በርካታ ተመራቂዎች እንደሚያስፈልጉ አቶ ደሳለኝ አመልክተዋል፡፡ በየትኛውም አገር በአብዛኛው የሚቀጠረው የተማረ የሰው ኃይል በግል ኢንተርፕራይዞች ወይም በራሱ በሚፈጥረው የሥራ ዘርፍ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፣መንግሥት የሚቀጥረው የተወሰነውን ብቻ እንደሆነና ተመራቂዎች በግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተቋማት እንደሚሰማሩም ገልጸዋል፡፡ከዚሁ ጎን ለጎን የመንግሥት ሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት እስከ ቀበሌ ድረስ መስፋፋቱና መንግሥታዊ ተቋማት ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማካሄዳቸው ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር አስችሏል፡፡ የግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በርካታ የአገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች በምርትና በአገልግሎት መስኮች ለመሰማራት እንዳስቻላቸውም አቶ ደሳለኝ ገልጸዋል፡፡፡ በመላው አገሪቱ ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪ ተነስተው ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ የተሸጋገሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ማህበራት መታየታቸውም ሥራን በመፍጠር ራስንና አገርን መጥቀም እንደሚቻል ሁነኛ ማሳያ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ ተመራቂዎች ”ሥራ አያገኙም” የሚለው አባባል አገሪቱ እያስመዘገበች ያለውን ፈጣን ዕድገት ባለመገንዘብና በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ብቻ መቀጠርን ዋነኛው አማራጭ አድርጎ ከመጠበቅ እንደሚመነጭም አመልክተዋል፡፡ በአገሪቱ እየተካሄዱ ካሉት በኢንዱስትሪ፣በኮንስትራክሽን፣በመሠረተ ልማት፣በቤቶች ግንባታና በሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ግዙፍ ፕሮጀክቶች ጋር ተያይዞ እየተፈጠሩ ያሉት የአገልግሎት መስኮች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰለጠነ የሰው ኃይል እንደሚያስፈልግም ያመላክታሉ፡፡ የአገሪቱ ኢኮኖሚዋን ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ መሪነት ለምታደርገው ሽግግርም በዕውቀት የተመሰረተ ኢኮኖሚውን የሚመራ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች እንደሚያስፈልጉም ዳይሬክተሩ አስረድተዋል። እንደ ኢዜአ ዘደባ አሁን ላሉና ወደፊት ለሚፈጠሩ የምርትና የአገልግሎት መስኮች የሚፈለገውን የሰው ኃይል በበቂ ሁኔታ ለማፍራት የተጀመረው የ70/30 የመስኮች ምጣኔ ትክክለኛ አቅጣጫ መሆኑን እንደሚያመለክት የዘገበው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ነው፡፡", "passage_id": "807590dd79e6858d4b787c4aeaa80fd7" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- የማህበረሰቡን ችግር መፍታት ላይ የሚያተኩር ‹‹ሶልቭኢት›› የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድር ከ1ሺ500 በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ ለሁለተኛ ጊዜ ትናንት በይፋ ተጀምሯል፡፡በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በተደረገ ይፋ የመክፈቻ ስነስርአት ላይ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማት እና ምርምር ዳይሬክተር ጀነራል የሆኑት አቶ ካሊድ አህመድ እንደተናገሩት፤ ተወዳዳሪዎቹ ጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም መሰረታዊ የማህበረሰብ ችግሮችን የሚፈቱ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በመስራት ይሳተፋሉ፡፡ በፈጠራ ባለሙያዎቹ የሚሰሩ ችግር ፈቺ ቁሶች ወደገበያው እንዲገቡ ለማድረግ እገዛ ይደረጋል፡፡በአይኮ ግላብስ ‹‹የሶልቪት›› የፕሮጀክት አማካሪ የሆነው ወጣት ህሩይ ፀጋዬ ውድድሩን አስመልክቶ እንደገለፀው፤ በኢትዮጵያ የተሻሻለ ቴክኖሎጂን በመፍጠር የማህበረሰብን ችግር የማቃለል ልምድ ወደኋላ የቀረ ነው፡፡ ቴክኖሎጂ ቅንጦት እና ለአደጉት አገራት ብቻ  የሚሰራ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በዚህ መነሻ የቀን ተቀን ችግር ለመፍቻ እና ኢንዱስትሪዎችን ለማዘመን ይህን ውድድር ማካሄድ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በሁሉም አገሪቷ የሚገኙ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ስልጠና በመስጠት እንዲሳተፉ ይደረጋል፡፡ ሃሳባቸውንም ገበያ ላይ ሊውል ወደሚችል የቴክኖሎጂ ውጤት እንዲቀይሩ ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡በሶልቭኢት የመጀመሪያ ዙር ውድድር ላይ የኦክስጂን ቴራፒ (በደም ውስጥ ያለውን የኦክስጂን መጠን የሚለካ) ቴክኖሎጂ፣ከባህላዊ መጠጦች ከሚገኝ ተረፈ ምርት ውጤት የኤሌክትሪክ ማመንጫ ቴክኖሎጂ እንዲሁም በተለያየ ምክንያት እቃዎችን እንዳንዘነጋ የሚያስታውስ ‹‹ሄሎ ሪማይንደር›› ቴክኖሎጂን የፈጠሩ ወጣቶች አሸናፊ ሆነዋል፡፡የሁለተኛው የሶልቭኢት ውድድር በ15 ከተማዎች የሚካሄድ ሲሆን አዲስ አበባ፣ አርባ ምንጭ፣ አክሱም፣ ድሬዳዋ፣ ጎንደር፣ ጋምቤላ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ውድድሩ ከመካሄዱ በፊት ሁሉም ተሳታፊዎች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር የሚቀይሩበትን መንገድ የሚያመላክት የድጋፍ ስልጠና ይወስዳሉ፡፡ ስራቸውን የሚያከናውኑበት የገንዘብ ድጋፍም ይደረግላቸዋል፡፡‹‹ሶልቭኢት›› የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድር  አሜሪካ ኤምባሲ፣ የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ እንዲሁም የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንደሚደግፉት ታውቋል፡፡አዲስ ዘመን ጥር26/2011ዳግም ከበደ", "passage_id": "050b29381ba95d929f8c84436b2df7bf" }, { "passage": "በኢትዮጵያ የወጣቶች የፈጠራና የአዳዲስ ግኝቶች ክህሎት እንዲዳብር የሚመለከታቸው አካላት መስራት እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በፈጠራ ዙሪያ ያተኮረ የወጣቶች የውይይት መድረክ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን እየተካሄደ ነው፡፡በመድረኩ ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር  ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ እንዳሉት፥ ባደጉ ሀገራት ወጣቶች በፈጠራና በአዳዲስ ግኝቶች አማካኝነት የየሀገራቱን የሃብት ቁንጮ እየተቆናጠጡ ነው፡፡በመሆኑም በኢትዮጵያ የአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገትን ለመደገፍ ወጣቶችን ማብቃት ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ነው ያሉት ሚኒስትሩ፡፡ ", "passage_id": "a91a0521df291b4a61ca14c09c7361a9" }, { "passage": "፦ ብሔራዊ የሥራ እድል ፈጠራ ስትራቴጂው የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ለይቶ እንደሚያግዝ ተገለጸ፡፡ከተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅትና የተባበሩት መንግሥታት የንግድ የልማት አማካሪ ጋር በመተባበር በተዘጋጀው ብሔራዊ የሥራ ፈጠራ ስትራቴጂ ሰነድ ዙሪያ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ላይ የፌዴራል አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ማስፋፊያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስፋው አበበ እንደገለጹት፣ ስትራቴጂው የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ለይቶ ለመደገፍ የሚያግዝ ነው ፡፡የአገሪቱ ትልቁ ጥያቄ የሥራ እድል መፍጠር ነው ያሉት ዳይሬክተሩ ከዚህ አንጻር ስትራቴጂው የሚኖረው ሚና ብዙ ጊዜ በማህበር ሥራ እድል በመፍጠር ላይ ያጠነጠነውን አካሄድ በተለየ መልኩ የሚያስኬድና የፈጠራ ሃሳብ ያለውን ሰው ጠንካራ ድጋፍ በማድረግና የተለያዩ ማበረታቻዎችን በመስጠት በሥሩ በርካቶችን እንዲያቅፍ የሚያደርግ፤ በዚህም ዘላቂነት ያለው የሥራ እድል መፍጠር የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል፡፡በብሔራዊ ደረጃ የተዘጋጀው የሥራ ፈጠራ ስትራቴጂ በተለያየ መንገድ ሲከናወን የቆየውን ሥራ የተጠናና ውጤታማ ለማድረግ ከየት ተነስቶ የት ይድረስ የሚለውን ለመለየት እንዲሁም የሌሎች አገሮችን ተሞክሮ ያቀናጀ በመሆኑ ውጤታማነቱ ከወዲሁ ያስታውቃል ፤በአሁኑ ወቅትም ሥራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ ወደ ትግበራ በሚገባበት ደረጃ ላይ ይገኛል እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ፡፡ሀብት የሚባለው መሬት፣ ውሃ፣ የሰው ጉልበትና ሌሎችም ናቸው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ አሁን ላይ ግን እነዚህ ነገሮች በሙሉ ወይም በከፊል የሌላቸው አገራት የሥራ ፈጣሪ ሰዎቻቸውን በመጠቀምና በመደገፍ ከዜሮ ተነስተው ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሰዋል፤ ኢትዮጵያንም በዚህ አካሄድ ተጠቃሚ ለማድረግ ስትራቴጂው ትልቅ አቅም እንዳለው ጠቁመዋል፡፡የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ጊዜያዊ ችግሮችን ለመፍታት የሥራ እድል መፍጠር አስፈላጊ ቢሆንም ጊዜያዊ ነው፤ ዘላቂ የሚሆነው ሥራ ፈጣሪ የሆኑ ወጣቶችን ለይቶ መደገፍ ሲቻል መሆኑን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡በተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የብሔራዊ ፕሮግራም ኦፊሰር ና የተቋሙ ተወካይ አቶ አሰግድ አዳነ እንዳሉት አገሪቱ ላይ ያለው የሥራ እድል ፈጠራ በየዓመቱ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡትን ሥራ ፈላጊዎች የማዳረስ አቅም የለውም፤ በመሆኑም የሥራ ፈጠራ ሁኔታው የኢንዱስትሪ ፓርኮችንና ሌሎችንም በማስፋፋት መሸፈን አለበት፡፡አዲስ ዘመን ሀምሌ\n17/2011", "passage_id": "01c94f02cdf3a1634c3b657880dd6c37" }, { "passage": "የኤልጂ-ኮይካ ሆፕ ኮሌጅ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ኤሌክትሮኒክስ ዘርፎች በደረጃ ሶስትና አራት ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ቅዳሜ እንደሚያስመርቅ አስታወቀ፡፡የሁለተኛ ዙር ተመራቂ ሰልጣኞች  ያዘጋጁትን የፈጠራ ውጤት በዓውደ ርዕይ መልክ ለጎብኝዎች ትላንት አቅርበዋል፡፡ዓውደ ርዕዩ በተከፈተበት ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘርኡ ስሙር ኮሌጁ ኢትዮጵያ በትኩረት እያከናወነችው ያለውን የቴክኖሎጂ ልማት በማገዝ አርአያነት ያለው ተግባር እያከናወነ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡የኮሌጁ አካዳሚክ ዲን አቶ ታሪኩ ገብረመድህን በበኩላቸው ስልጠናው የሚሰጥባቸው ዘርፎች ለሥራ ፈላጊዎች በቀላሉ ሥራ ፈጥሮ ወደ ገበያው ለመግባት የሚያስችሉ በመሆናቸው ሰልጣኞቹ ውጤታማ እንደሚሆኑ ገልጸዋል፡፡የኤልጂ ቢሮ ዳይሬክተር ዩን ሆ ኪም ደግሞ ሰልጣኞቹ በየኛውም የዓለም ክፍል ሊሰሩበት የሚያስችል ዓለምአቀፍ ክህሎትና እውቀት እንዳገኙ ተናግረዋል፡፡ ለማሳያነትም ከተመራቂዎቹ መካከል ስድስቱ ከሀገር ውጭ ለስራ መቀጠራቸውን ገልጸዋል፡፡የኤፍኤም ማሰራጫ፣ ምስልና ድምጽ ማጫዎቻ፣ በዲጂታል ሲስተም የሚሰራ ኃይል ቆጣቢ ምጣድ፣ የእግረኛና የመኪና ፍጥነት መቆጣጠሪያ መሳሪያ እና የውሃ ብክነት መከላከያ መሳሪያ ተመራቂ ተማሪዎቹ ከሰሯቸው ችግር ፈቺ መሳሪያዎች መካካል በአውደርዕዩ ላይ ቀርበዋል፡፡በዓውደ ርዕዩ ላይ ስድስት የኮሪያ ደርጅቶች መሳተፋቸውንም ታውቋል፡፡ተማሪዎች ስልጠናውን እየተከታተሉት የሚገኙት በነፃ እንደሆነና የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎች ቁጥር 51 ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 13ቱ ሴቶች ናቸው፡፡ ", "passage_id": "19ef07a6dc2446420575b284a9ca79bd" } ]
5971ad77a1e692760ec9962f40ba90ee
c7d2e7b06fd49ca0109706283a3ab606
ተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ህዝቡ መጪው ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና መላው የአገሪቱ ህዝብ ወደ እውነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰዱ የአገራዊ ለውጥ እርምጃዎችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መጪው ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በውጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ የብልጽግና ፓርቲ ጥሪ አቀረበ። የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ከታህሳስ 8 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን መደበኛ ስብሰባ አጠናቅቋል። በጉባኤው ማጠናቀቂያ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ብልጽግና ፓርቲ =በመጪው ምርጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ በውጤታማነት እንዲያጠናቅቅ በሚያስችሉት ጉዳዮች ላይ መክሮ አቅጣጫ አስቀምጧል። በአገሪቱ በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለምርጫው ውጤታማነት እና በህዝብ ዘንድ ተአማኒነት ኖሮት እንዲጠናቀቅ በማድረግ በኩል የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ማበርከት ይኖርባቸዋል። ፓርቲው ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፤ የፓርቲው ማዕከላዊ በሰላም፣ በልማት፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና መጪውን አገራዊ ምርጫ በተመለከቱ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል። በዋናነት ባለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል በኢትዮጵያ የታየው ለውጥ በርካታ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፈተናዎችን ተጋፍጦ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ ሰፊ እድል የፈጠረና አገራችንን ከብተና አደጋ ያዳነ መሆኑ በውይይቱ ከስምምነት ተደርሷል። በተለይም ብልጽግና ውሁድ ህብረ ብሄራዊ አገራዊ ፓርቲ ሆኖ መደራጀቱ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ከፍተኛ እድል ከመፍጠሩም በላይ ከአገሪቱ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ተገለው የዳር ተመልካች የነበሩ በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ለማቀፍና ለማሳተፍ የቻለ የመጪው ትውልድ ፓርቲ መሆኑ ተረጋግጧል። በአገራዊ ለውጡ የተገኙ ድሎችን ጠብቆ በማስቀጠል ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የተገለጸ ሲሆን ለዚህም የፓርቲውን መርሆዎች፣ እሴቶችና አሰራሮችን በጥብቅ ዲሲፕሊን ተግባራዊ ማድረግና ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መገንባት አስፈላጊ መሆኑ ከስምምነት ተደርሷል። ከዚህ በተጓዳኝ፣ ኮሚቴው በሁለቱ ቀናት መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን አቅጣጫዎች አስቀምጧል። ከእነዚህ መካከል አንዱ የቀጣዩን ምርጫ የሚመለከት ሲሆን፤ ብልጽግና ፓርቲ በመጪዉ ምርጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ በውጤታማነት እንዲያጠናቅቅ በፓርቲው ማኒፌስቶ ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አጽድቆታል። መላው የፓርቲው አመራሮችና አባላት የጸደቀውን ማኒፌስቶ መሰረት በማድረግ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተቀምጧል። በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ እውነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰዱ የአገራዊ ለውጥ እርምጃዎችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መጪው ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በውጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል። መላው የአገሪቱ ህዝቦች ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት በኢትዮጵያ የታዩ ለውጦችና የተገኙ ድሎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ መጪው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅና የዜጎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልጽግና የተረጋገጠባት ጠንካራ አገር ለመገንባት በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽዖ ሁሉ እንዲያደርጉም ነው ፓርቲው ጥሪውን ያስተላለፈው።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37697
[ { "passage": " አዲስ አበባ፦\nይህ ትውልድ በዘመኑ\nየተጋረጡበትን ጉልህ አደጋዎች\nበፍፁም ህብረ ብሔራዊነት\nለመመከት ከምንጊዜውም በላይ\nአንድነቱን አንዲጠብቅ የትግራይ\nብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ\nአመራር ዶክተር አብረሃም\nበላይ  ጥሪ አቀረቡ። በሀገር ብሔራዊ ጥቅም ላይ እጃቸውን ለማስገባት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን አጥብቆ እንዲኮንንም አሳስበዋል።የግንቦት 20 በዓልን በማስመልከት ዶክተር አብረሃም በላይ ባስተላለፉት መልክዕት እንዳስታወቁት፣ ይህ ትውልድ በዘመኑ የተጋረጡበትን ጉልህ አደጋዎች በፍፁም ህብረ ብሔራዊነት ለመመከት ከምንጊዜውም በላይ አንድነቱን እንዲጠብቅና የነገዪቱን ሰላማዊት፣የለማችና በአንድነቷ የጠነከረች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ አበክሮ በመስራት የድል ብስራቱን ወደ አዲስ አውድ እንዲያሸጋግር ጥሪ አቅርበዋል።የአገራችን ሕዝቦች በትውልድ ቅብብሎሽ በታሪክ ካጋጠሟቸው የሉአላዊነት አደጋዎችና ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በሕይወት መስዋዕትነትም ጭምር በተከፈለ ውድ ዋጋ አልፈው የዛሬዪቱን ኢትዮጵያ አስረክበውን በክብር አልፈዋል ያሉት ዶክተር አብረሃም፣ ሀገራችን በዘመናት ሒደት ያጋጠሟት እነዚህ ልዩ ልዩ ፈተናዎች ለእያንዳንዱ ትውልድ ልዩ የዚያ ዘመንና ትውልድ ታሪካዊ ተልዕኮዎችና የቤት ሥራዎች መሆናቸውን ስንገነዘብም የአሁኑ ትውልድ ዘመኑን መርምሮና ዋጅቶ ሊፈፅማቸው ስለሚገቡ ዘመን ተሻጋሪ የታሪክ ተልዕኮዎቹ ቆም ብሎ ሊጠይቅና ሊያስተውል እንደሚገባው በመገንዘብ ነው ብለዋል።\nየግንቦት 20 በዓል አከባበር ፋይዳና ተምሳሌትነትም በአብዛኛው በታሪክ በተለምዶ የ60 እና የ70ዎቹ ትውልድ ተብሎ የሚታወቀው ትውልድ በሕዝቦች ላይ ይደርስ የነበረውን የመብት ረገጣ፣ ጭቆና፣ ግፍና አፈና ለመቀልበስ ዘመኑ የሰጣቸውን ታሪካዊ ተልዕኮ በመስዋዕትነት በመወጣት የፈፀሙትን ታሪካዊ ገድል በክብር የምንዘክርበትና የመስዋዕትነቱንም ፍሬ ለሕዝቦች መብት መከበርና ጥቅም መረጋገጥ ባስገኘው ተጨባጭ ውጤት ላይ እውነተኛ የህሊና ዳኝነት እየሰጠን ሊሆን እንደሚገባ አመልክተዋል።ይህ ትውልድም በዚህ ዘመን ልዩ የሆነ የታሪክ ተልዕኮ ያለው ነው ያሉት ከፍተኛ አመራሩ፣ ከፊቱም በርካታና ውስብስብ ችግሮች እንደተደቀኑበት ጠቅሰዋል። በተለይም ሁለንተናዊ ቀውስ በዓለማችን ብሎም በሀገራችን በማስከተል የሚገኘውና በፍጥነት በመዛመት ላይ ያለው የኮሮና ቫይረሰ ወረርሸኝ ትልቅ የአደጋ ስጋት መሆኑን ጠቅሰዋል።በሽታው በሀገራችን ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተደገፉ ልዩ ልዩ የመከላከልና ስርጭቱን የመቆጣጠር እርምጃዎች በመንግሥት በኩል ቢወሰዱም አጥጋቢ ውጤት ባለመገኘቱ ሌሎች ጠንከር ያሉ እርምጃዎች መውሰድ የምንገደድበት ሁኔታ ውስጥ እንደምንገኝ መንግሥት ይፋ ማድረጉን ጠቁመው፣ ይህ የህልውና ስጋት የሆነብን ችግርም ከምንጊዜውም በላይ የበለጠ መረዳዳትና የጋራ አቋም የሚፈልግ ነው ብለዋል። በመንግሥት በኩል ከሚወሰዱ\nእርምጃዎች በተጨማሪ ኅብረተሰቡ\nግንዛቤውን በማጥራት በመንግሥትና\nሌሎች የተረጋገጡ ምንጮች\nየወረርሽኙን ስርጭት ለመቆጣጠርና ለመከላከል\nየሚሰጡ የጥንቃቄ ምክሮችን\nማድመጥና ያለመታከት መተግበር\nእንደሚያስፈልግ መክረዋል።ይህ ትውልድ በሌላ ግንባር ከከፈታቸው የጥቃት ርምጃዎች አንዱና ዋነኛው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክታችን ግንባር ቀደም ተጠቃሹ እንደሆነ ያመለከቱት ዶ/ር አብረሃም ፣ በዚህ የትግል አውድም ሕዝባችን ከጅማሬው አንስቶ ለፕሮጀክቱ የከፈለውና በመክፈል ላይ የሚገኘው መስዋዕትነትም በታሪክ በመጪው ትውልድ የሚወሳ እንደሆነም አመልክተዋል።የግድባችን ጉዳይ በአሁኑ ወቅት ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚሰነዘሩ ግልፅና ስውር ትንኮሳዎች ቢኖሩበትም ሕዝብና መንግሥታችን ርትዕ ሕግና ፍትሐዊ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማያረጋግጡ ድምፆች ጆሮ ሳይሰጥና ሳይዘናጋ በመሬት ላይ ያለውን ነባራዊ ሀቅ በተግባር ለመቀየር የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ይገኛል ብለዋል።መላው ሕዝባችን ይህንን ጉዳይ በልዩ ትኩረት እንዲከታተለውና በሀገር ብሔራዊ ጥቅም ላይ እጃቸውን ለማስገባት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን አጥብቆ እንዲኮንን አሳስበዋል። የግንቦት 20 በዓልንና የበዓሉን ትርጉም በማጣጣም ሕዝባችን ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ ታሪክ በድጋሚ እንደሚፅፍ ያለኝን ጠንካራ እምነት ስገልፅ በዓሉ የደሰታና የሰላም እንዲሆንልን ከልቤ በመመኘትም ጭምር ነው ብለዋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 21 ቀን 2012 ዓ.ም በጋዜጣው ሪፖርተር", "passage_id": "8adb6a4aeeff0f3a42fcccc3b0388551" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2013 (ኤፍቢሲ) የትግራይ ህዝብ በስሙ ሲነግዱ የነበሩ የህወኃት አመራሮችን በማጋለጥ ከአገር መከላከያ ሰራዊት ጎን እንዲቆም የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ትዴፓ/ ጥሪ አቀረበ። በህወኃት ውስጥ ያሉ ቡድኖች በሕገ-መንግሥትና በፌዴራል ሥርዓት አልገዛም በማለት ከመሀል አገር ሸሽቶ መቐለ ከመሸገ ወዲህ የትግራይ ወጣቶችን እየሰበሰበ ”በልዩ ሀይል”ሥም ሲያደራጅ፣ ሲያሰለጥንና ሲያስታጥቅ መክረሙንም ትዴፓ በመግለጫው አመልክቷል። አመራሮቹ እነዚህን ወጣቶች በመላ ሃገሪቱ በማሰማራት በንፁሐን ዜጎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸምና በኢትዮጵያ አለመረጋጋት እንዲነግስ በማድረግ ወደ ሚናፍቁት ስልጣን የመመለስ ፍላጎት አላቸው ብሏል። ጥቂት የህወኃት ቡድኖች በሃገር አንድነትና በህዝቦች ህልውና ላይ እየፈጸሙ ያለውን የሽብር ጥቃት መንግስት ለትግራይ ህዝብ ሲል በሆደ ሰፊነት ማለፉ ለህዝቡ ያለውን ወገንተኝነት የሚያሳይ መሆኑንም ጠቅሷል። ”የህወኃት አመራር ለ29 ዓመታት መላው የኢትዮጵያ ህዝብን ረግጦና በዝብዞ ገዝቷል” ያለው መግለጫው የትግራይ ህዝብ ያተረፈው የእነርሱን መጥፎ ስም ብቻ መሆኑን ነው አጽንኦት የሰጠው። የትግራይ ህዝብ መከራ እንዲያበቃ በስሙ ሲነግዱ የነበሩ የዴሞክራሲ፣ የሠላምና የአንድነት ጠላት የሆኑት የህወኃት አመራሮችን በማጋለጥ ወገንተኝነቱን ካረጋገጠው የመከላከያ ሠራዊት ጎን መቆም እንደሚገባም አሳስቧል። መንግሥትም ይሁን የአገር መከላከያ ሠራዊት ለትግራይ ህዝብ ሲባል ያሳየውን ጥንቃቄና ሆደ-ሠፊነት የሚደገፍ ቢሆንም፤ የህወሓት አመራር ላይ ተገቢውን እርምጃ መውሰዱ ለአገር አንድነትና ለወገን አለኝታነት ሲባል የሚደገፍ ነው ብሏል ትዴፓ በመግለጫው። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የትግራይ ህዝብ የህወሓት አመራር ክፉ አገዛዝ ሠለባ መሆኑን በመገንዘብ በጋራ ትግል ለጋራ ድል ለመብቃት ለሚደረገው ጥረት ተባባሪ እንዲሆን ትዴፓ ጥሪ ማቅረቡን ኢዜአ ዘግቧል። ", "passage_id": "be9fe78ece91542ae3b85a605fb0e050" }, { "passage": "በሚቀጥለው አመት ለሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ መንግሥት የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት፣ የምርጫና የተለያዩ የህግ  የማሻሻል እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛል፡፡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሰብሰብ ብለው ጠንካራ ተፎካካሪ እንዲሆኑ እንደሚያግዛቸው ቃል ተገብቶላቸዋል፡፡ መንግሥት እየፈጠረ ያለውን ምቹ ሁኔታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዴት እየተጠቀሙበት ነው? የመንግሥት እገዛንስ እንዴት ያዩታል?የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ሊቀመንበር ዶክተር አረጋዊ በርሄ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲና የሀሳብ ነጻነት እንዳልነበር በማውሳት፣ በሀገር ውስጥና በውጭ በሚኖር ህዝብ ግፊትና በጥቂት የፖለቲካ ሰዎች የተገኘውን ለውጥ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸው ይገልጻሉ፡፡ መድረኩ ከተከፈተ ያላቸውን ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አመለካከትም ለህዝቡ በማስተላለፍ መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ይናገራሉ፡፡ ዕድሉ ህዝቡ የሚሻለውን ለመምረጥ ምቹ ሁኔታ ፈጥሮለታል ይላሉ፡፡እንደ ዶክተር አረጋዊ በርሄ ማብራሪያ ምቹ ሁኔታ ቢኖርም ሁሉም እኩል እየተጠቀመበት ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡ በአመለካከትም በአደረ ጃጀትም ዥንጉርጉር  ነገር ነው የሚስተዋለው፡፡ ከፊሉ የብሄር፣ከፊሉ ደግሞ ሀገርአቀፍ ሆኖ  ነው የሚንቀሳቀሰው፡፡ አንዳንዱ ለመጠቀም ጥረት ሲያደርግ ሌላው ደግሞ አክራሪና ለዘብተኛ ሆኖ ወዳልተገባ አቅጣጫ እያመራ ነው፡፡ እነዚህን የተለያዩ አመለካከቶች በተፈጠረው የሃሳብ ነፃነት ለኢትዮጵያ የሚጠቅመውን አቅጣጫ ለመከተል ውይይቶች እየተካሄዱ ነው፡፡‹‹መንግሥት ነፃነቱን ሰጥቶናል፡፡ቀሪው የእኛ የቤት ስራ ነው››ሲሉም ገልጸዋል፡፡የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁጥር እንዲቀንስ በመንግሥት እየተሰጠ ያለውን ሃሳብ እንደሚደግፉ የሚናገሩት ዶክተር አረጋዊ የፓርቲዎች ቁጥር መብዛት ህዝብን ከማወናበድ አልፎ ፓርቲዎችን እንደሚያስጨንቅና ከአምስት ፓርቲ በላይ መብለጥ እንደሌለበትም አመልክተዋል፡፡ ‹‹ፓርቲዎች የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው ዓላማቸውን ማሳካት እንጂ መንግሥት እርምጃ እንዲወስድ የሚገፋፋ ተግባር መፈጸም አይገባም›› በማለት ጫና ከሚፈጥር ተግባር መቆጠብ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አበበ  በበኩላቸው እንዳሉት፤ በውጭ ሆነው ሲታገሉ የነበሩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገር ውስጥ ገብተው ሰላማዊ የሆነ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ በመንግስት የተወሰደውን እርምጃ ፓርቲያቸው በመልካም ጎኑ ይመለከተዋል፡፡ «ለሁለት አስርት አመታት ስንጮህበት የነበረውን ምላሽ እያገኘን ነው፡፡ ከኢህአዴግ አምባገነናዊ ስርአት አኳያ የተሻለ ነገር እያየን ነው፡፡ መንግሥትን እናመሰግናለን » ብለዋል ፡፡«የተፈጠረውን ዕድል በአግባቡ ካልተጠቀ ምንበት ከእጃችን የማይወጣበት ምክንያት የለም፡፡ ወደ ኃይል ከገፋነው ኢህአዴግ ለአምባገነንነት ቅርብ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰው ናቸው፡፡ ኢህአዴግም ናቸው፡፡ በድርጅቱ ውስጥም ያደጉ ናቸው›› በማለት ፓርቲዎች ወደኃይል ከመግፋት ይልቅ ዕድሉን እየደገፉ ለተሻለ ነገር ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው አስረድተዋል ፡፡ዕድሉ ቢኖርም ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ለምርጫ ምቹ ሁኔታ አለ ብሎ ፓርቲያቸው አያምንም፡፡ የሀገሪቷ መረጋጋትና የዜጎች በህይወት የመኖር መብት መረጋገጥ አለበት፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ተፈናቅለው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው የምረጡን የምርጫ ኮሮጆ ይዞ መቅረብ ተገቢ ነው ብሎ ፓርቲያቸው እንደማያምንና ህዝቡ በአካባቢውና በቀዬው መምረጥ  እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡ሰላሙን ለማረጋጋት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሚና ቢኖራቸውም የአንበሳውን ድርሻ መንግሥት መውሰድ አለበት፡፡ሀገርን የሚያናጋ ነገር ሲፈጠር በልበ ሰፊነት መታለፍ የለበትም፡፡ እርምጃ መወሰድ አለበት፡፡ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ዋጋ የተከፈለው ኢትዮጵያ የጥቂቶች መኖሪያ እንድትሆን አይደለም፡፡ በውይይትና በድርድር እየተባለ የመንግሥትና የህዝብ ህልውና መጣስ የለበትም፡፡ ኢህአዴግ አምባገነን የማይሆንበት ምክንያት የለም፡፡ መንግሥት ማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ ትኩረት ማድረግ አለበት በማለት አክለው ገልፀዋል፡፡ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁጥር መቀነስ ጋር ተያይዞ ለሚቀርበው ሃሳብም አቶ ሙሉጌታ‹‹ ገዥው ፓርቲ የፈጠራቸው ፓርቲዎች አሉ፡፡ ይህን መፈተሽ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ በአዋጅ የመቆጣጠር ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡በዚህ መሰረት እነማን መስፈርቱን እንደሚያሟሉ መለየትና ህጋዊ መሰረት ማስያዝ ይችላል፡፡ምርጫ ቦርድ ልጆቹን የማያውቅ አባት ሆኖ ነው የቆየው››ሲሉም ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡ ፓርቲያቸውም ከሰፈርና ከጎጥ ካልወጡ ፓርቲዎች ጋር መደራደር አይፈልግም ብለዋል፡፡ወደ አንድ መምጣትንም ፓርቲያቸው እንደሚደግፍ፤ ነገር ግን ወደአንድ ሲመጣ ፓርቲያቸው ህልውናውን ጠብቆ ግንባር ሊፈጥር ይችላል በማለት ገልጸዋል፡፡‹‹መንግሥት ለምርጫው እየፈጠረ ያለውን ምቹ ሁኔታ ጅምሩን ገና እያየን ነው፡፡ተጀመረ እንጂ እልባት አላገኘም››በማለት ሃሳባቸውን የሰጡት የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ)ሊቀመንበር ዶክተር መረራ ጉዲና፤ ከምርጫ ቦርድ ጋር ስምምነት ተፈጥሮ ገና ወደማዋቀር አልተገባም፡፡አዋጅም ገና አልወጣም፡፡ሌሎች ህጎችም በጥናት ላይ ናቸው፡፡ውይይቶችም እየተካሄዱ ነው፡፡እነዚህ ሁሉ  ባሉበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ለማለት አያስደፍርም ብለዋል፡፡ከምርጫ ጋር ተያይዞ በመንግሥት ላይ ይሰነዘር የነበረው ወቀሳ አሁን ወደ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች  ዞሯል ስለሚባለው ጉዳይ ዶክተር መረራ በዚህ ደረጃ ላይ እንዳልተደረሰና አሁንም ኳሱ በመንግሥት ሜዳ ላይ ነው ሲሉ ለአስተያየቱ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ዶክተር መረራ ችግር ውስጥ የገቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የማስተካከል ኃላፊነት የመንግሥት ድርሻ እንደሆነና በሀገሪቷ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁጥር  ከ10 እንደማይበልጡ ፣80 የሚባለው ገዥው ፓርቲ የሚያውቃቸው እንደሆኑና እራሱ መለየት እንዳለበት ተናግረዋል፡፡አዲስ ዘመን ጥር 3/2011ለምለም መንግሥቱ ", "passage_id": "e3b77b45a3405346860ac44f9456c1f1" }, { "passage": "ምርጫው መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ያኮራ ሰላምና ጨዋነት የሰፈነበት  የዴሞክራሲ ስርዓት መጎልበትን የሚያሳይ ጤናማ ምርጫ እንደነበርም ተናግረዋል።ለሂደቱ ጤናማ መሆን የሕብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ እንደነበር የገለጹት ሚኒስትሩ ባለፉት ምርጫዎች የሰጠው ድምጽ ዋጋ እንደነበረው በመረዳቱ ከምዝገባ ጀምሮ እስከ ምርጫው ማጠቃለያ ድረስ ለምርጫው ሰላማዊነት ያላሳለሰ ጥረት አድርጓል ብለዋል።የመራጩ ህዝብ ድምጽ ተደምሮ ይፋ የሚሆነው ውጤትም እስካሁን የነበረው ሰላማዊ ሂደት አካል እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ሬድዋን ሁሴን  ከዚህ በኋላ  የሚፈጠር  አፍራሽ ተግባር እንደማይኖር እምነታቸውን ገልጸዋል።አምስተኛው ጠቅላላ ምርጫው ስኬተማ ሆኖ እንዳይጠናቀቅ አንዳንድ አካላት ጥረት ሲያደርጉ ቢቆዩም በህዝቡ የነቃ ተሳትፎ እንዲሁም ለሁሉንም ዜጋ በሚያኮራ መልኩ ምርጫው  በስኬትና  በአስደማሚ ሁኔታ  መከናወኑን  ተናግረዋል ።በአገሪቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ  የምርጫ ሂደት እያዳበረና እየጎለበተ  መምጣቱ  በተግባር  5ኛው ዙር  ጠቅላላ ምርጫ አረጋግጧል ያሉት አቶ ሬድዋን በትናንትናው ዕለት ሥርዓቱን ጠብቆ የተከናወነው  የድምጽ አሠጣጥ  ሂደት ትልቅ  ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል ።ምርጫውን  ምንም አይነት ሰበብ መደርደር የማያስችል በመሆኑ  የመራጩ ህዝብ ውሳኔ ተከብሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ሚኒስትሩ  ስኬቱ የሁሉም ዜጎች  የጋራ ጥረት ውጤት በመሆኑ ህብረተሰቡ ላሳየው ጨዋነት መንግስት ምስጋናውን ያቀርባል ብለዋል።", "passage_id": "88accbb9a95b4d869aa9300013e3e0f1" }, { "passage": "ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የበሩባቸውን ድክመቶች  አስወግደው የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው የፌደራል መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈትቤት አስገነዘበ ፡፡የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ከመሥራት አኳያ የነበሩባቸውን ድክመቶች አስወግደው በሚዘጋጁት መድረኮች የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የአገሪቷን ሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ለማገዝ ቁርጠኝነታቸውን ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው ጽሕፈትቤቱ ባወጣው ሳምንታዊ የአቋም መግለጫ አስገንዝቧል ።ዜጎች በፈለጉት የፖለቲካ ድርጅት ታቅፈው መንቀሳቀስ የሚችሉበት፣ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መጎልበት ወሳኝ ሚና ያላቸው የፖለቲካ ድርጅቶች ተመስርተው በህጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱበት ሁኔታ መፈጠሩን በመጥቀስ ።ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በአገሪቷ በተካሄዱ ምርጫዎች ሁሉ እየተካፈሉ የሚገባቸውን ያህል የምክር ቤት ወንበሮች ሲይዙ መቆየታቸውንም አንስቷል ፡፡ይሁንና ባለፉት ሁለት ምርጫዎች የገዢው ፓርቲ ሙሉ የበላይነት የተከሰተበት በመሆኑ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ተሳትፎ ተገድቦ እንደነበር አመልክቷል ።በመሆኑም መንግሥት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ተረጋግቶ እንዲቀጥል ካለው ፍላጎት በመነሳትና በአገሪቷ ያለውን የፍላጎት ብዝሃነት ይገነዘባል ነው ያለው መግለጫው ፡፡ስለሆነም ወሳኝ የሥልጣን አካል የሆኑት የህዝብ ምክር ቤቶችን የተለያዩ ድምጾች የሚሰማባቸውና የሚፎካከሩባቸው መድረኮች ማድረግ እንደሚገባ አቋም መውሰዱን በማስታወስ ።ይህም መንግስት ዴሞክራሲያዊ መድረኮችን በማስፋት በሰላማዊ ፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ውይይት፣ ድርድርና ክርክሮች ማካሄድ ብሎም ህጎችን እስከማሻሻል ድረስ መሄድ እንዳለባቸው ቁርጠኝነቱን ማሳየቱን ነው የጠቀሰው ።ከዚህ አንጻር ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሰላማዊ እስከሆኑ ድረስ የሚሳተፉባቸውን መድረኮች እያመቻቸ መሆኑን አስረድቷል ።ዛሬ አገሪቷ የምትመራበትን ህገ መንግሥት በማርቀቅ ሂደት የፖለቲካ ፓርቲዎች የየራሳቸውን አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን እንደማይዘነጋ በመግለጽ  ።አገሪቷ የመድበለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መከተል ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገቧን መግለጫው አውስቷል።", "passage_id": "e16e946474c7f312d79369ad2fef7674" } ]
a32c82d913b3aed4dfcd668fce1da06d
cefcbd11c14200d02727eeb3f417b151
«በአገራችን ሰፊውን ህዝብ በአግባቡ ሊያንቀሳቅሱ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አልተፈጠሩም»ዶክተር ዲማ ነገዎ የፖለቲካ ምሁር
አስቴር ኤልያስ አዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ ሰፊውን ህዝብ በአግባቡ ሊያንቀሳቅሱ እና ሊያነሳሱ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገና አልተፈጠሩም ሲሉ የፖለቲካ ምሁሩ ዶክተር ዲማ ነገዎ ተናገሩ። ዶክተር ዲማ፣ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ በአገሪቱ አንዱ እና ትልቁ ችግር የፖለቲካ አደረጃጀት ጉዳይ ነው። በዚህም እስካሁን ሰፊውን ህዝብ ሊያንቀሳቅሱ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር አልቻሉም።“በአገራችን እስካሁን ድረስ የፖለቲካ ቡድኖች እንጂ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሉም” የሚሉት ዶክተር ዲማ፤ ከዚህም የተነሳ “ሰፊውን ህዝብ በአግባቡ ሊያንቀሳቅሱ እና ሊያነሳሱ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገና አልተፈጠሩም” ብለዋል።በቀጣይ በአገራችን የተሻለ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲፈጠር የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር መቻል አለባቸው የሚል እምነት አለኝ ያሉት የፖለቲካ ምሁሩ ዶክተር ዲማ፤ ለዚህ ምክንያታቸው ደግሞ በአገሪቱ ያሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች በትክክል የህዝብን ፍላጎት ያገናዘበ እንቅስቃሴ ሲያድርጉ ባለመታየታቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸውለማለት የማያስችል በመሆኑ እንደሆነ አመልክተዋል።እንደ ዶክተር ዲማ ገለጻ፤ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ መሆን የሚጠበቅበት የሕዝቡን ልዩ ልዩ ጥቅም የሚያንጸባርቅ እንጂ የተወሰነውን ቡድን ስሜት ብቻ የሚከተል መሆን የለበትም። ስለዚህ ሰፋ ያለውን የህዝቡን ፍላጎት የሚያንጸባርቁ የፖለቲካ ድርጅቶች መፈጠር አለባቸው። እስካሁን ያሉት በቡድን ደረጃ ነው። ስለሆነም ትልቁ የሚቀረው ነገር ቢኖር በትክክል የተዋቀሩና ህዝብን መሰረት ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር እንደሚኖርባቸው ማወቅ ነው። ለተቋማት መገንባት ደግሞ ሰፋ ያለ ፍላጎት ላይ የተመሠረቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያስፈልጋሉ።በኢትዮጵያ ውስጥ የተረጋጋ እና ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ስርዓት ለመገንባት ቢያንስ ገለልተኛ የሆነ የአገሪቱን እና ህዝቡን የሚያገለግል የመንግሥት ስርዓት መኖር አለበት የሚለውም ጉዳይ ሊተኮርበት እንደሚገባ የሚናገሩት ዶክተር ዲማ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በስርዓት መገንባት እና መደራጀት እንዳለባቸው ገለጸዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37768
[ { "passage": "ወጣቶችን ማሳተፍ፣ ወደ አመራር ማምጣት በየመድረኩ የሚጠቀስ ዓለም አቀፍም ሀገራዊ ጉዳይ ነው፡፡ ወጣቶች በህብረተሰቡ ውስጥ ካላቸው ብዛት አኳያ  ነው መሳተፍም፣ ወደ አመራር መምጣትም አለባቸው የሚባለው፡፡ይህ ወጣቶችን የማሳተፍ እና ወደ አመራር የማምጣት አስፈላጊነት በፖለቲካ ፓርቲዎች በኩልም ዘወትር ይነሳል፡፡ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ባለፈው ባካሄዱት ድርጅታዊ ጉባኤያቸው ነባር የአመራር አባላትን በክብር ሲያሰናብቱ ወደ ሥልጣን ካመጧቸው ወጣቶች መካከል ይገኙባቸዋል፡፡ወጣቶችን ወደ አመራር ከማምጣት አኳያ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ክፍተት እንዳለባቸው የተለያዩ ወገኖች ይጠቁማሉ፡፡ የፓርቲዎቹ መሥራቾችና ነባር አመራሮች የአመራር ስፍራውን ለዘመናት ይዘውታል፤ ወጣቶችን ወደ አመራር ለማምጣት ሲሠሩ አይታዩም እየተባሉም ይተቻሉ፡፡የተፎካካሪ ፓርቲዎች በበኩላቸው ለዓመታት የተደረጉብን ጫናዎች ወጣቶችን ለማብቃትና ወደ አመራር ለማምጣት ቀርቶ፣ በአባልነትም ይዞ ለመሥራት የማያስችሉ ነበሩ ሲሉ ምላሻቸውን ይሰጣሉ። የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበብ ወጣቱን በፖለቲካ ውስጥ እንዳይሳተፍ የሚያደርግ፣ ቢሳተፍም ከፍተኛ መስዋዕት የሚያስከፍል እንደነበር ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ይጠቁማሉ።አንጋፋው ፖለቲከኛና የተፎካካሪ ፓርቲ መሪ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ‹‹የቆየንበት የፖለቲካ ድባብ ወጣቶችን ለማብቃትና ወደ ኃላፊነት ለማምጣት የሚጋብዝ አልነበረም››ይላሉ፡፡ በእኛ ሀገር ዐውድ የፖለቲካ ፓርቲ -አመራር መሆን ማለት ራስን ለማይገባ መስዋዕትነት ማጋለጥ ነው ሲሉም ሀገሪቱ ያሳለፈቻቸውን አፋኝ የፖለቲካ ዓመታት ይገልጻሉ፡፡አውራውን ፓርቲ ለመቀናቀን አመራር መሆን ቀርቶ አባል መሆን በራሱ ለከፋ  ተፅዕኖ ሲዳርግ መቆየቱን፣ ይህም ተጨባጭ ሁኔታ ወጣቱ ወደ ፖለቲካው መድረክ እንዳይመጣ ማድረጉን ያስታውሳሉ፡፡‹‹ወጣቱ ሥራ ይፈልጋል፤ ሥራ ላይም መቆየት ይፈልጋል››ያሉት ፕሮፌሰር በየነ፣ ተፅዕኖዎቹ ወጣቱ ለመድረክ እንዲበቃ ደንቃራ እንደነበሩ ያብራራሉ፡፡ ወጣቶች ምቹ ሁኔታ ከተፈጠረላቸው  የአመራር ቦታውን ለመቀበል ምን ጊዜም ዝግጁ መሆናቸውንም ነው የሚጠቁሙት።የፖለቲካ ሳይንስ ምሁርና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዴን) ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ‹‹ያሳለፍናቸው ዘመናት ወጣቱን መስዋዕትነት ውስጥ የሚከቱ እንጂ ለፖለቲካ ፓርቲ አባልነት የሚያበቁ አልነበሩም›› በማለት የፕሮፌሰር በየነን ሀሳብ ያጠናክራሉ፡፡ በሀገር ውስጥ በአመራርነት ቀርቶ በአባልነት ለመሳተፍ የሚቻልበት ሁኔታ እንዳልነበር ይጠቁማሉ። በዚህ የተነሳም ወጣቱን ለማብቃት የሚያስችሉ ዐውዶች አልነበሩም ይላሉ።ፕሮፌሰር መረራ በውጭ ሀገሮች ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ወጣቱን የሚያሳትፉ እንዳልነበሩ ይጠቅሳሉ፡፡ ከፖለቲካ ፓርቲዎቹ መካከል በውጭ ሀገሮች ከ40 እስከ 50 ዓመት የቆዩ እንዳሉ ጠቅሰው፣ ተተኪ አመራሮችን ለማፍራት እንደሚቸገሩ ይናገራሉ፡፡ ‹‹በውጭ የሚኖሩ ወጣት ዜጎቻችን ለእንጀራቸው ስለሚሮጡ በፖለቲካ ውስጥ ለመሳተፍ ሊቸግራቸው ይችላል›› ሲሉ ፕሮፌሰር መረራ ይጠቁማሉ፡፡ወጣት ምሁራንን ማፍራት እንደሚገባም አስገንዝበው፣ መጪው ዘመን በሀገር ውስጥ ምቹ ሁኔታዎች ሊፈጠሩ የሚችሉበት ስለመሆኑ ፍንጮች እየታዩ መሆናቸውንም ያመለክታሉ፡፡ ወጣቶችን ማፍራት የሚቻልበት ሜዳ ሠፊ እና ምቹ እንደሚሆንም ይገልጻሉ።የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ አመራር አቶ ተሻለ ሰብሮ ከሁለቱም ፖለቲከኞች የተለየ ሀሳብ ነው ያላቸው፡፡ ፓርቲው ሲዋቀር አንስቶ በወጣቶች የተሞላ መሆኑን፣ ከ3ሺህ አባላቱ 2/3ኛው ወጣቶች መሆናቸውን ያብራራሉ።ወጣት አባላቱ ራዕይ ያላቸው ሀገር ተረካቢ እንዲሆኑ ከአንጋፋዎቹ የአመራር አባላት ተሞክሮዎቹን እንዲቀስሙ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተሻለ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወጣት አባላትንና አመራሮችን ለማፍራት ጥረት አያደርጉም የሚለው ፓርቲያቸውን እንደማይመለከት ይናገራሉ፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚያነሱት ወጣቶችን ወደ አመራር የማምጣት ጉዳይ ፓርቲው ሲመሰረት አንስቶ በሕገ ደንቡ በግልፅ አስፍሮ ሲሠራበት የቆየ መሆኑን ነው ።የፓርቲያቸው አመራሮች የሥራ ዘመን አራት ዓመት መሆኑን የሚናገሩት አቶ ተሻለ፣ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ለሁለት ዙር መመረጥ የሚቻልበት ዕድል እንዳለም ይናገራሉ፡፡ ከሁለት ዙር በላይ ማገልገል ግን እንደማይቻል ይጠቁማሉ፡፡አመራሩ አዲሱን አመራር ተቀብሎ ኃላፊነቱን ያስረክባል። በቀጣይ ፖለቲካውን በሰከነ መንገድ የሚመሩ የተማሩና ልምድ ያላቸው ወጣቶችን ለማብቃት እየሠራን ነው ይላሉ፡፡የፖለቲካ ሥልጣን ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጥበት መሆኑን ጠቅሰው፣ በፓርቲያቸው ውስጠ ዴሞክራሲ መሰረት ይህን ኃላፊነት የሚወጡ ብቃት ያላቸውን ወጣቶች በአመራርነት ለማስቀጠል እየተሠራ መሆኑን ይጠቁማሉ።‹‹በኃላፊነትና በሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውስጥ ወጣት ኃይል ነው ያሰባሰብነው፤ ወጣት ምሁራንም አሉበት፤ አንድ ሁለት የሚሆኑ መካከለኛና አንጋፋ ዕድሜ ላይ የሚገኙ አመራሮች ያሉበት ነው›› ሲሉ አቶ ተሻለ  ይናገራሉ።አቶ ተሻለ ቀደም ሲል ስጋትና የመሳሰሉት ተግዳሮቶች እንደነበሩ አስታውሰው፣ በሴቶች እና ወጣቶች ላይ ብዙ ለመሥራት ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ይገልጻሉ፡፡ አሁን የተፈጠረው ምቹ የፖለቲካ ምህዳር በወጣቱ ዘንድ የፖለቲካ ተሳትፎ ፍላጎት  ማሳደሩንም ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2011 በኃይለማርያም ወንድሙ", "passage_id": "03629b6dea606ae984bc6dd5fb3a476a" }, { "passage": "በአገሪቱ የመጣውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ የሚታየውን አለመረጋጋት ግምት ውስጥ በማስገባት አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምርጫው በተያዘለት መርሐግብር መካሄድ አለበት ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫው መራዘም አለበት የሚል አቋም አላቸው፡፡ በአንጻሩ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በተያዘለት የጊዜ መርሐ ግብር ለማካሄድ ሽር ጉድ እያለ ይገኛል፤ በዚህ ስጋትና ተስፋ በተጋረጠበት ምርጫ 2012 የመገናኛ ብዙኃን ሚና ምን ሊሆን ይገባል? ደበበ ኃይለገብርኤል የህግ ቢሮና የናሽናል ኢንዶውመንት ፎር ዴሞክራሲ የተባሉ ተቋማት “የአገራችን መገናኛ ቡዙኃን ሚና ለዳበረ ዴሞክራሲያዊ ሂደት በኢትዮጵያ” በሚል በቅርቡ ከስድስት ብሮድካስት የመገናኛ ብዙኃን ላይ 88 ዘገባዎችን በናሙናነት በመውሰድ የዳሰሳ ጥናት አካሂደው ነበር፡፡ ጥናቱ በአገሪቱ የመጣውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ የተከሰቱ ግጭቶችን የሚዲያ ተቋማት በምን መልኩ ዘገቡት የሚለውን ያሳየ እንደነበር በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙዩኒኬሽን ትምህርት ክፍል መምህር ፍሬዘር እጅጉ ይናገራሉ። መምህር ፍሬዘር እንደገለፁት፤ የጥናቱ ውጤት እንደሚያሳየው መገናኛ ብዙኃኑ የግጭት ዘገባዎችን ሲዘግቡ ወገንተኝነት፣ ስሜታዊነትና ጽንፈኝነት የሚታይባቸው ነበሩ። እንዲሁም ለተፈጠሩ ችግሮች መፍትሄ ከመጠቆም አንጻር አሉታዊምና አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደነበራቸው አመላክቷል፡፡ በተለይ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱና ተቋማዊ መፍትሄ እንዲያገኙ አቅጣጫ ከመስጠት በተጨማሪ መንግሥትን ተጠያቂ በማድረግና ለዜጎች ወቅታዊ መረጃዎችን በመስጠት በጎ የሆነ አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ በጥናቱ ተመላክቷል። በአንጻሩ የሚፈጠሩ ችግሮችን ተባብሮ በመስራትና በመቻቻል መፍታት ያስፈልጋል በሚለው ላይ በስፋት እንደመፍትሄ ወስደው እንዳልሰሩ በጥናቱ መመላከቱን የገለፁት መምህር ፍሬዘር ገልጸው፤ ከዚህ አንጻር መገናኛ ብዙሃኑ ስለትናንትና ግጭት ዘገባዎቻቸው ሲያነሱ፤ እርቅና አንድነትን በሚያመጣ መልኩ አላወሱትም ብለዋል። ከዚያ ይልቅ ውስጣዊ ክፍፍልን በሚፈጥር መልኩና ትናንት በጭቆና ውስጥ ነበርን የሚል ብያኔ በመስጠት የተጠመዱበት ሁኔታ ነበር ይላሉ። በአጠቃላይ ጥናቱ እንደሚያሳየው መገናኛ ቡዙኃኑ ገለልተኛ ተቋም ሆነው ተወዳዳሪና ተገዳዳሪ የሆኑ የተለያዩ አመለካከቶችን ባለማስተናገዳቸው የተለያዩ ቡድኖች፣ አንጃዎች፣ ብሄሮችና ፖለቲካ ፓርቲዎች መታገያና ፕሮፓጋንዳ መንዣ ሜዳ መሆናቸውንና የአገርን ህልውናና የህዝብን ጥቅም እንዳላስቀደሙ በዕለት ተዕለት ትግበራቸው አሻራቸው በግልጽ መቀመጡን ገልጸዋል። መምህር ፍሬዘር እንደገለፁት፤ አንድ ምርጫ ግልጽ፣ ተዓማኒና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የአንበሳውን ደርሻ ከሚጫወቱ ተቋማት መካከል የመገናኛ ቡዙኃን ሚና አይተኬ ነው። መገናኛ ብዙኃኑ በምርጫ ወቅት በብዙ መልኩ አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ ቢችሉም፤ በምርጫው የመጀመሪያ ግባቸው ገለልተኛ ሆነው ከጽንፈኝነትና ስሜታዊነት ተላቀው ትክክለኛና አስተማማኝ መረጃን ለዜጎች በማቅረብ መረጃ ያነገበ ዜጋ መፍጠር ይገባቸዋል። በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ፤ የመገናኛ ቡዙኃ ን ለህብረተሰቡ ያላቸውን ወገንተኝነትና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ከሚያሳዩበት ወርቃማ አጋጣሚዎች ግንባር ቀደሙ የምርጫ ወቅት ነው ይላሉ። ስለዚህ ምርጫው ፍትሃዊ፣ ነጻና ግልጽ ሆኖ ሀሳቦች በነጻነት ተወዳድረው ህዝብ ያመነበት መንግሥት ወደ ስልጣን እንዲመጣ፤ የመገናኛ ብዙኃኑ ከወገንተኝነት እራሳቸውን አላቀው፣ የሚነቀፈውን በመንቀፍ የሚበረታታውን በማበረታታት፣ ጥያቄ የሚያስነሱ ጉዳዮችን ከሚመለከተው አካል ተገቢውን ማብራሪያ በመጠየቅ ለማህኅበረሰቡ ግልጽ በማድረግ ማኅበረሰቡ ምርጫው ላይ እምነት እንዲኖረው እና በነቂስ ወጥቶ እንዲመርጥ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ይናገራሉ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በካሪኩለም እና ኢንስትራክሽን ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር እንጉዳይ አደመ በበኩላቸው፤ አሁን በአገሪቱ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የመገናኛ ብዙኃኑ በሁለት ጎራ የቆሙ ሲሆን፤ በአንድ ወገን የቆሙት መንግሥት ምንም አይነት ህፀፅ እንደሌለበት በጎ በጎውን ያወራሉ። በሌላኛው ጽንፍ የቆሙት ደግሞ እንከንን ብቻ በማራገብ የመከፋፈል ሥራ ይሠራሉ። ስለዚህ መጪውን ምርጫ በተመለከተ በሁለት ጽንፍ የቆሙት የመገናኛ ብዙኃን ተቀራርበው በመስራት ፍታሃዊ ሆነው የምርጫ ሂደቱን መዘገብ አለባቸው። በዘገባውም የአገርን ህልውና የህዝብን ጥቅም ማስቀደም ይገባቸዋል ይላሉ። በሚዘግቡበት ወቅትም ጥላቻንና ግጭትን በሚያጭር ሁኔታ ሳይሆን ህዝብና ህዝብን በሚያቀራርብ መልኩ መዘገብ እንደሚገባቸው ፕሮፌሰሯ አሳስበዋል። በአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት\nእንዲጎለብትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን\nመገናኛ ቡዙኃኑ ኃላፊነት\nእንደተጣለባቸው የሚናገሩት መምህር\nፍሬዘር ፤ በምርጫ\nሂደቱ አጨቃጫቂ ጉዳዮች\nሲኖሩ እራሳቸውን ገለልተኛ አድርገው ነገሩን ከስር ከመሰረቱ መርምሮ እውነታውን ለህዝብ በማሳወቅ እና አለመግባባቶች በሰከነ ሁኔታ የሚፈቱበትን መንገድ ማመላከት አለባቸው ይላሉ። መገናኛ ቡዙሃኑም በራቸውን ለአንዱ ክፍት ለሌላው ዝግ ሳያደርጉ ፤የሁሉንም የፖለቲካ ሀይሎች ሀሳብ ማስተናገድ የሚጠበቅባቸው መሆኑን መምህር ፍሬዘር ይናገራሉ። የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ በበኩላቸው፤ የመገናኛ ብዙኃን ከምረጡኝ ቅስቀሳ ጀምሮ ምርጫው ተጠናቆ በህዝብ የተመረጠ መንግሥት ወደ ስልጣን እስኪመጣ ድረስ ያለውን ሂደት ደረጃ በደረጃ ለኅብረተሰቡ መረጃ በመስጠት ግንዛቤ እንዲኖረው ማድረግ አለባቸው። በሌላ በኩልም ከዚህ ቀደም ምርጫ ላይ ተሳትፈው የማያውቁና ወደ መራጭነት የዕድሜ ክልል ለሚቀላቀሉ ወጣቶች ስለምርጫ ስርዓትና ህግ ግንዛቤ መፍጠር ይጠበቅባቸዋል። በምርጫ ቦርድና በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን አዋጅ አንቀጽ 44 እና 43 ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው፤ በምርጫ ወቅት የመገናኛ ብዙኃኑ ነጻ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ አምዶችን እየመደቡ እጩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀሳቦቻቸውን ለኅብረተሰቡ እንዲሸጡ ድምጽ ሆነው ማገልግል አለባቸው። ባለፉት አምስት አገራዊ ምርጫዎች ላይ በከፍታም በዝቅታም ውስጥ እያለፉ የተሻለ የምርጫ ዘገባ በመስራት የተሻለ ምርጫ እንዲካሄድ ልምድ ያዳበሩ አንጋፋ መገናኛ ብዙሃን መኖራቸው ይታወሳል። ከምርጫው ከኋላ እየተከተሉ አቃቂር ማውጣትና ጉድለቶቹን ማራገብ ሳይሆን፤ ከፊት እየቀድሙ አቅጣጫ እየሰጡ ሂደቱን መምራትና አደናቃፊ ሁኔታዎችን ከወዲሁ በመቅረፍ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲካሄድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ እንደሚገባም ዶክተር ጌታቸው አሳስበዋል። ምሁራኑ እንደሚሉትም፤ መገናኛ\nቡዙሃኑ በምርጫ ሂደቱ\nበከፍተኛ የኃላፊነት ካልዘገቡ\nትናንሽ ግጭቶች ጎልተው\nወደ ቀውስ በመቀየር\nአገር ሊናጋ የሚችልበት\nእድል ሰፊ ነው።\nበአንጻሩ ምርጫው ተቋማቱ\nለአገርና ለህዝብ ጥቅም\nዘብ መቆማቸውን የሚያሳዩበት\nወርቃማ ዕድል በመሆኑ፤\nይህንን አደራ በከፍተኛ\nየኃላፊነት ስሜት መወጣት\nከቻሉ የኢትዮጵያን የፖለቲካ\nታሪክ በመቀየር የዴሞክራሲያዊ\nስርዓት ግንባታ ዋልታን\nየሚተክሉበት አጋጣሚ ላይ\nእንደሚገኙ ምሁራኑ ይናገራሉ።አዲስ ዘመን ታህሳስ 29/2012ሶሎሞን በየነ", "passage_id": "2826b80938ce18817a5d9749ddf1521e" }, { "passage": "በኢትዮጵያ የግዛት አንድነት ቢኖርም በሕዝብ ስምምነት የተፈጠረ ብሔራዊ አንድነት አለመኖሩን አንዳንድ የፖለቲካ አባላት ገለፁ። ገዥዎች የፈጠሩት እንጂ ሕዝቦች ተመካክረው በስምምነት ያመጡት አስተዳደራዊ መዋቅር እንደሌለም ተናግረዋል፡፡ የኦሮሞ ነፃነት\nግንባር\nማዕከላዊ\nኮሚቴ\nአባልና\nየሕዝብ\nግንኙነት\nኃላፊ\nአቶ\nቀጀላ\nመርዳሳ፤\n‹‹ኢትዮጵያ\nእንደአገር\nየተመሰረተችው\nቅርብ\nጊዜ\nነው።\nከተመሰረተች\nበኋላ\nየግዛት\nአንድነት\nቢኖርም\nበሕዝብ\nስምምነት\nየተፈጠረ\nብሔራዊ\nአንድነት\nየለም።\nሕዝቦች\nተመካክረው\nበስምምነት\nያመጡት\nአስተዳደራዊ\nመዋቅርም\nየለም።\nገዥዎች\nለራሳቸው\nእንዲመቻቸው\nያደረጉት\nነው››\nብለዋል።\nእንደ አቶ\nቀጀላ\nማብራሪያ፤\nበኢትዮጵያ\nሕዝብ\nለሕዝብ\nበጉርብትናና\nበአንድነት\nአብሮ\nመኖር\nእንጂ\nበመዋቅር\nደረጃ\nብሔራዊ\nአገራዊ\nአንድነት\nየለም።\nበ1983\nዓ.ም ሕዝቦች ቁጭ\nብለው\nበመወያየት\nብሔራዊ\nአንድነት\nለማምጣት\nሞክረዋል።\nሆኖም\nየተሟላ\nአልሆነም።\nዴሞክራሲያዊ\nሥርዓት\nአልተፈጠረም።\nኢኮኖሚውና\nፖለቲካው\nበአንድ\nቡድን\nእጅ\nየወደቀ\nነበር።አቶ ቀጀላ\nአገራዊ\nአንድነት\nለማምጣት\nበሕዝቦች\nመካከል\nእኩልነት\nመስፈን\nእንዳለበት፤\nዴሞክራሲ\nሥርዓት\nመፈጠርና\nየብሔረሰቦች\nመብት\nመከበር\nእንደሚኖርበት፤\nይህ\nከሆነ\nአብሮ\nመኖር\nእንደማያስቸግር፤\nይህን\nማድረግ\nየእያንዳንዱ\nብሔረሰብና\nዜጋ\nኃላፊነት\nእንደሆነ፤\nአንድነት\nእንዲመጣም\nየዜጎች\nኃላፊነት\nእንደሚያስፈልግ\nጠቁመዋል።\n‹‹ከዚህ በኋላ በኢትዮጵያ የአንድ ቡድን አስተሳሰብ አይሰራም፤ አገሪቱን ይበትናል፤ ሁሉም ሰላምን፣ ነፃነትና አንድነትን ማዕከል በማድረግ የአገሪቱን አንድነት መስመር ማስያዝ ይገባል። ይህን ለማድረግም ተስፋው በሕዝብ እጅ ነው››ሲሉም አክለው ይናገራሉ። የአማራ\nብሔራዊ\nንቅናቄ\nሊቀመንበር\nዶክተር\nደሳለኝ\nጫኔ\nበበኩላቸው፤\nበኢትዮጵያ\nብሔራዊ\nአንድነት\nእንደሌለ፤\nበታሪክ\nአረዳድ፣\nበትርክቶች፣\nበብሔራዊ\nጀግኖችና\nበምልክቶች\nመግባባት\nላይ\nእንዳልተደረሰ፤ ለዚህ ትልቁ ችግርም ያልተስተካከለ የታሪክ ምልከታና ብያኔ መሆኑን ያስረዳሉ። እንደ ዶክተር ደሳለኝ ማብራሪያ፤ ሕዝቦች ለዘመናት አብረው አንፀባራቂ ድሎችን አስመዝግባዋል። በግንኙነታቸው ውስጥም መልካምም መጥፎም ገጠመኞችም ነበሯቸው። ከ1960ዎቹ ወዲህ የተፈጠሩ ብሔረተኞች የችግሮቹ መንስዔና በዳይ አድርገው ጨቋኝ ተጨቋኝ በማለት የተሳሳተ የታሪክ ብያኔ ይሰጣሉ። ይህ በስህተት ላይ የተመሰረት ብያኔ አገራዊ መግባባት እንዳይፈጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል። ዶክተር ደሳለኝ ‹‹አገራዊ መግባባት እንዲፈጠር የታሪክን አረዳድ ማስተካከል። በአገሪቱ የተፈጠረው ልማትም ሆነ ጥፋት የሁሉም ሕዝቦች የጋራ አድርጎ መውሰድ ይገባል። በውሸት ላይ የተመሰረቱና የተመረጡ የታሪክ ንባቦችን ማረም። ፖለቲከኞች ባለፈ ታሪክ ከመነታረክ ወጥተን ለልጆቻችን መልካም አገር ለማውረስ የቀጣይ የ50 ዓመታት የጋራ ርዕይ በማስቀመጥ ወደ ሥራ መግባት አለብን፤ ታሪክን ለፖለቲካ መሣሪያና ትርፍ ከመጠቀም መቆጠብ ያስፈልጋል›› ብለዋል። ይህን ተግባራዊ ለማድረግ\nበርካታ ባለድርሻዎች አሉ።\nየፖለቲካ ኃይሎች ግን\nያለፈ ታሪክ ላይ\nከመነታረክ ወጥተን የኢትዮጵያ መጽዒ ዕድል ላይ በጋራ መፍትሄ መፈለግ አለብን ያሉት ዶክተር ደሳለኝ፤መንግሥት፣ የታሪክ ምሁራንና የማህበረሰብ አንቂዎች የተሳሳቱትን አካሄዶች ማስተካከል ላይ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ‹‹በኢትዮጵያ ብሔራዊ መግባባት የለም። የዚህ መንስዔ ሊሂቃኑ ላለፉት ሃምሳ ዓመታት ጥያቄ ቢያነሱም ወደ ብሔራዊ መግባባት አልደረሱም። አገርን የሚመሩ ድርጅቶችና ተቀናቃኝ ኃይሎች ብሔራዊ መግባባት ላይ አልደረሱም። ልሂቃኑ ህልማችውን ይዘው ፍጅትና ግጭት በመፍጠር ከመቆዘም ያለፈ ራሳቸውን ለውጠው ሕዝብን በመለወጥ ብሔራዊ መግባባት ማምጣት አለመቻላቸው ዋና ምክንያት ሆኗል›› ይላሉ። እንደ ፕሮፌሰር መረራ\nገለፃ፤ አገራዊ መግባባት\nለመፍጠር ሁሉም የቤት\nሥራውን መስራት አለበት፤\nበቀዳሚነት አገርን የሚመሩ\nአካላት ሕዝብን በማቀራረብ\nብሔራዊ አንድነት መፍጠር\nአለባቸው፤ ከሴራ ፖለቲካ\nመውጣትና የፖለቲካ ምህዳሩን\nማስፋት ይኖርባቸዋል፤ ተቀዋሚዎችም\nቢሆኑ ህልማቸውን እያስታመሙ አገሪቱን ከመበጥበጥ የሰከነ ፖለቲካ በማራመድ በደረጃ የቤት ሥራቸውን መስራት አለባቸው፤ ዳር ቆሞ ፖለቲካውን እየቆሰቆሱ አገርን ከመጉዳት ወደ ሀቀኛ የፖለቲካ ድርድር መግባት አለባቸው፤ ዳር ቆሞ እያራገቡ ሕዝቡን ለግጭት ከመዳረግ መቆጠብ አለባቸው፤ ሁላችንም ኃላፊነት መወጣት አለብን፤ ከፖለቲካ ውጪ ያሉ ልሂቃንም ሕዝቡን የማስተባበር፣ የማንቃት፣ የማደራደር ሥራ መስራት አለባቸው፤ ለሥልጣን ብሎ አገሪቱን ከመተብተብ ከችግር ለማውጣት በመስራት አገራዊ መግባባትን መፍጠር ይገባል። የአፋር ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር ሊቀመንበር መሀሙድ ጋአስ፤ አገራዊ መግባባት ለመፍጠር ጽንፍ የወጡ አካሄዶች መታረም እንዳለባቸው፤ ጽንፈኝነት ለማንም እንደማያዋጣ፤ በተለያዩ ጽንፍ ያሉ አካላት ሰጥቶ በመቀበል መርህ ወደ መሀል በመምጣት ብሔራዊ አንድነት መፍጠር እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል። ሊቀ መንበሩ ‹‹ጽንፍ\nየወጡ አስተሳሰቦችን ለማለዘብ\nሕገ መንግሥቱን፣ ህብረ\nብሔራዊነትንና የብሔር ብሔረሰቦችን\nመብት የሚያከብሩ አካላት\nወደ አንድ መምጣት\nአለባቸው፤ የአገሪቱን መጻዒ\nዕድል የተሻለ ለማድረግም\nበጋራ መስራት ያስፈልጋል››\nብለዋል።አዲስ ዘመን ጳጉሜ 6/2011አጎናፍር ገዛኸኝ", "passage_id": "b7a6f2c175db8db33f1263a83f36fd5f" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2006 (ዋኢማ) – በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ምህዳር በህጋዊ መልክ ለሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችም   እየሰፋ መምጣቱን አቶ አባይ ጸሃየ ገለጹ።የፖሊሲ ጥናትና የጠቅላይ ሚኒሰትሩ አማካሪ ሚኒሰተሩ አቶ አባይ ፀሀየ ለዋኢማ እንደገለፁት  በህገመንግስቱ ጥላ ስር ለሚንቀሳቀሱ ሐይሎች የፖለቲካ ምህዳሩ ከመቸውም በተሻለ ሁኔታ ሰፍቷል።ከሽግግር ጊዜ ጀምሮ በርካታ አሳታፊ ህጎች በማርቀቅና በመተግበር ራሱም ለሕጎቹ ተገዢ በማድረግ ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ለምርጫ ተወዳዳሪነት በመቅረብ ስልጣን የያዘ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አባይ ጸሃየ  ኢህአዴግ ማንኛውም የፖለቲካ  ፓርቲ በህዝብ ይሁንታ ስልጣን የሚይዝበትን  በቂ የፖለቲካ ምህዳር መፍጠሩን ገልጸዋል። እንደ አቶ አባይ ጸሃየ በአገሪቱ ያሉት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የቂም በቀልና  የዘረኝነትና  ፖለቲካ የሚያናፍሱ እንጂ ለአገር ልማት የቆሙ አይደሉም።  የኢህዴግ ትግል ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ለመፍጠር ስለሆነ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ሕገመንግስቱን አክብረውና ህዝብንና አገርን  የሚጠቅም ፖሊሲና ስልት መያዝ ይኖርባቸዋል ብለዋል።የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝብን አሳታፊ ፖሊሲ ከነደፉና በህጋዊ መልክ ከተንቀሳቀሱ የፖለቲካ ምህዳሩ ሰፊ ለእነዚህ አካላት የፓርቲካ ምህዳሩ ይሰፋል እንጂ አይጠብም ብለዋል።አቶ አባይ አያይዘውም በህገወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ድርጅቶች መወዳደር የሚፈውድ ሕግ  በአውሮፓም ይሁን በአመሪካ እንደሌለም አቶ ኣባይ ተናግረዋዕ።የኢህአዴግን ጥቃቅን ድክመቶች  እየለቃቀሙ የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል የሚል ሰበብ በመደርደር የራሳቸውን ስህተት ከመሸፈን ይልቅ ህጉን አክብረውና አስከብረው  የፖለቲካ አላማቸውን ማራመድ ይበጃቸዋል ብለዋል።ሕጋዊነትንና አመጽን  እያጠቃሱ መራመድ  ለህዝብም ሆነ ለአገሪቱ  አይጠቅምም ያሉት ሚኒስትር አባይ  ተቃዋሚዎች ከዚህ የጥፋት ስልት ተላቀው የሁሉንም ህዝብ ጥቅምና መብት የሚስከብር ፖሊሲ መከተል  ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። የሀገር ፍቅር ያለው፣  ሐላፊነትን የሚሸከምና  ታማኝ  ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት የአገሪቱ ኢኮኖሚ እየጎለበተ ሲሄድ ይፈጠራል የሚል እምነት እንዳላቸውም ገልጸዋል።", "passage_id": "d445cf0a2a4d713917025052fb219147" }, { "passage": "‹‹ዘንድሮ የሚካሄደው ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?›› የሚል ጥያቄ የሚያነሱ ብዙዎች ናቸው። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሚኒኬሽን አማካሪ ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ እንደምትገልፀው ቦርዱ እስከ አሁን 139 ፓርቲዎችን መዝግቧል። ከእነዚህ መካከልም ለመወዳደር የሚያበቃ መስፈርት አሟልተው በቦርዱ የእውቅና የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው 68 ብቻ ሲሆኑ ቀሪዎቹም በሂደት ያሟላሉ ተብለው ይጠበቃሉ። ‹‹ላለፉት አምስት ዙሮች ከተካሄዱት የምርጫ ተሞክሮዎች አኳያ በመስከረም ወር የሚጠበቅ ዝግጅት የለም›› የምትለው ሶሊያና ከዚህ በኋላ ግን የምርጫ ዝግጅት መርሃ ግብሮች በቅደም ተከተል ይከናወናሉ። በአዲስ አደረጃጀት ሥራውን በማከናወን ላይ ያለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፉት ስምንት ወራት ካከናወናቸው ተግባራት መካከል የማስፈፀም አቅሙን ለማሳደግ የወሰዳቸው እርምጃዎች ቀዳሚ ሲሆኑ፣ በአሠራር የሚጠበቅበትን ተግባር በተሻለ ለመፈፀም አሁንም በሰው ኃይልና በአሠራሩ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው ብላለች።የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በምርጫ ቦርድ በኩል ፍጥነት ያለው ሥራ እየተሠራ ነው ብለው አያምኑም። በነበረው ተሞክሮ በዚህ ወቅት አልፎ አልፎ ድርድሮች እንደሚካሄዱ፣ ቦርዱም የጊዜ ሰሌዳውን ስለሚያሳውቅ ፓርቲዎች የቦርዱን መረጃ መሰረት አድርገው እንደሚያንቀሳቅሱ ያስታውሳሉ። ቦርዱ አሁን ባለው እንቅስቃሴው የወሰደው የማሻሻያ እርምጃና የአደረጃጀት ለውጥ ወረዳ ላይ አልደረሰም። የፀደቀው የምርጫ ምዝገባና የሥነ ምግባር አዋጅ በአንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቀባይነት አላገኘም ሲሉ ይገልፃሉ። የፕሮፌሰር መረራ ጉዲናን ሀሳብ የሚጋሩት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ ቦርዱ በአዲስ አደረጃጀት መዋቀሩና እስካሁንም ባከናወናቸው ተግባራት የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን ማዘጋጀቱን በመልካም ጎን የሚያዩት ቢሆንም የተሟላ በቂ ዝግጅት አድርጓል ለማለት አልደፈሩም። በዚህ ወቅት ቦርዱ አስፈፃሚዎችን የማደራጀት ተግባር አጠናቅቆ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የምርጫ ሰሌዳ ሊያውቁ የሚገባበት ወቅት መሆን ነበረበት ያሉት አቶ ናትናኤል ቦርዱ መዋቅሩን በየወረዳዎች አለመዘርጋቱ በጊዜ ሰሌዳው ተጽዕኖ እንደሚኖረው እንደምክንያት ያነሳሉ። የሚከናወነው ሥራ ምርጫ ለማካሄድ ብቻ መሆን እንደሌለበትና እውነተኛ ለሆነ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሽግግር መደላድል መፈጠርና ከዚህ ቀደም በምርጫው ላይ ይነሱ የነበሩ ቅሬታዎችን የሚያስቀር መሆን እንዳለበት ያምናሉ።ፕሮፌሰር መረራ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያሉት የፀጥታ ችግሮችም ለምርጫው ሥጋቶች እንደሆኑና ችግሮች የሚታዩባቸውን ምዕራብ ኦሮሚያ፣ ጉጂና ቦረና አካባቢዎችን ይጠቅሳሉ። በገዥው ፓርቲ በኩል ለምርጫው ያለው ዝግጁነት ግልጽ ሆኖ አለመታየትና ገመድ ጉተታ የሚመስል ነገር በአባል ድርጅቶች መካከል መኖር እንዲሁም ከሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር አብረው ለመሥራት ያላቸው ፍላጎት ገና ብዙ ሥራ እንደሚፈልግ ያስረዳሉ። ክፍተቶቹም ምርጫው ይካሄድ የሚሉና አይካሄድ የሚሉ ሀሳቦች እንዲፈጠሩ ምክንያቶች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።አቶ ናትናኤልም ሀሳቡን በማጠናከር መንግሥት በሀገሪቷ ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንዲካሄድ ዝግጁነቱን በፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በኩል አረጋግጧል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም ያለማንም ሦስተኛ ወገን ጣልቃገብነት በጋራ ተስማምተው በፈረሙት የቃልኪዳን ሰነድ መሰረት እንቅስቃሴያቸው በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ መሆን አለበት ሲሉ መክረዋል።የኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሚያደርገው የምርጫ ዝግጅት ውጤታማ የሚሆነው ሰላም በሀገሪቷ ውስጥ ሲረጋገጥ እንደሆነ ያሰምሩበታል። ‹ደጋፊ ስላለ ብቻ ሳይሆን ሀገር ስትኖር ነው ምርጫ የሚካሄደው። ሰላም በሌለበት ስለምርጫ ለማውራት ከባድ ነው› በማለት ፓርቲያቸውም በሀገር ደረጃ ሰላም ላይ መሠራት እንዳለበት እንደሚያምን ተናግረዋል።ወይዘሪት ሶሊያና በበኩሏ ምርጫው ፍትሐዊ፣ ግልጽና ተአማኒ እንዲሆን የሚከናወኑት የማሻሻያ ተግባራት ያልተቋረጠ መሆን እንዳለበት ቦርዱ ቢያምንም ለህዝብ መረጃ ከመስጠት ጀምሮ እስካሁን የተሠሩትን ሥራዎች በስኬት ያነሳሉ። የቦርዱ ግብም ምርጫው በመራጩ ህዝብ ተአማኒነት እንዲኖረው፣ ነፃና ሰላማዊ እንዲሆን ማስቻል እንደሆነም ትናገራለች። አስተያየት ሰጭዎቹ እንዳሉት ምንም አይነት ሥጋት ቢኖርም ሀገራዊ ምርጫ መካሄዱ ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነ ያምናሉ። በመሆኑም ከምርጫው ዝግጅት ውስጥ ሰላም ትልቅ ቦታ ካልተሰጠው አጨራረሱ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።አዲስ  ዘመን መስከረም 29/2012 ለምለም መንግሥቱ", "passage_id": "27adefecd682165c72c4869818296682" } ]
612b053c9ebd6066e900ca753c02c5bf
28bfce8ecda1f44c6ec0c854ffb2f66e
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ከምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አደረጉ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን በትዊተር ገጻቸው ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ38ኛው አስቸኳይ የኢጋድ የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ጅቡቲ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ በትዊተር ገጻቸው እንዳሰፈሩት፤ በ38ኛው አስቸኳይ የኢጋድ የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ጅቡቲ መግባታቸውን ተከትሎ፤ ከሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሓምዶክ፣ ከሶማሊያው ፕሬዚዳንት መሀመድ ፋርማጆ፣ ከኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት ሬቤካ ንያዴግ ዲ ማቢዮር ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። መሪዎቹ ጁቡቲ እየተካሄደ በሚገኘው 38ኛው አስቸኳይ የኢጋድ የመሪዎች ጉባዔ ላይ የተሳተፉ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድም ከመሪዎቹ ጋር የተናጠል ውይይት አካሂደዋል። በዚህም የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና ከሶማሊያው ፕሬዚዳንት  መሀመድ ፋርማጆ በተናጥል ካነጋገሯቸው በኋላ፤ ሁለቱን መሪዎች በአንድ ላይ በማምጣት አነጋግረዋል። ይሄንንም ‘’ከመሪዎቹ ጋር በአካባቢያችን አንገብጋቢ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በጠረጴዛ ዙሪያ በመወያየታችን ደስ ብሎኛል’’ ሲሉ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የገለጹት። በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ የሚመራው የጉባዔው ተሳታፊ ልዑክ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ሲሆን፤ ጉባዔውም በአፍሪካ ቀንድ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳይ እንዲሁም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ዙሪያ የሚመክር ይሆናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12 ቀን 2013  ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37764
[ { "passage": "ከ28ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም እና ፕሬዚዳንት ኤል ሲሲ የተናጠል ውይይት ያደረጉት።ሁለቱ መሪዎች በአምስት ነጥቦች ላይ ውይይት በማድረግ የጋራ አቋም ይዘዋል።መሪዎቹ በሀገራቱ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር እስካሁን የተገኙ መልካም ዲፕሎማሲያዊ ድሎችን ለማጉላት እንደሚጠቅሙና የሁለትዮሽ መተማመን ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተስማምተዋል።ሁለትዮሽ ቀጠናዊ የትብብር መስኮችን ማስፋት እና ማጠናከር በተለይም በፖለቲካ፣ ሰለማና ፀጥታ፣ በኢኮኖሚ ዘርፍ ያሉ ትብብሮችን ማጉላት እንደሚገባ፤ ሁለትዮሽ ግንኙነትና ወንድማማችነትን የሚጎዳ ማንኛውንም አይነት ክስተት መቆጣጠርና መገደብ እንደሚገባም ነው ከስምምነት ላይ የደረሱት።መሪዎቹ ታላቁ የህዳሴ ግድብን አስመልክቶ የሶስትዮሽ የቴክኒክ ኮሚቴ ውይይቶችን እየተከታተለ እንደሆነና ግድቡን አስመልክቶ ያላቸውን  በትብብር መንፈስ የመስራት ቁርጠኝነት አድሰዋል።የመረጃ ልውውጥን ማሳደግ፣ የሁለትዮሽ ግንኙነትንና የጋራ ጉዳይ በሆኑ ቀጠናዊ እና አለማቀፋዊ ጉዳዮች በመሪዎች እና በተቋማት ደረጃ ተከታታይነት ያለው ምክክር እንዲካሄድም መሪዎቹ ተስማምተዋል።ከዚህም ባለፈ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትና በህዝቦች መካከል መተማመንን ለማሳደግ እንደሚያስፈልግ ለዚህም የመገናኛ ብዙሃን ሚና ወሳኝ መጫወት እንዳለባቸው ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም እና ፕሬዚዳንት ኤል ሲሲ የተስማሙት።መሪዎቹ በቋሚነት በተለያየ ጊዜ በሁለቱ ሀገራት ጉብኝት እንደሚያደርጉም ከመግባባት ላይ ደርሰዋል።በዚህ አጋጣሚም ፕሬዚዳንት ኤል ሲሲ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም በቅርቡ በግብፅ ጉብኝት እንዲያደርጉ ጋብዘዋቸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ከሱዳን ፕሬዚዳንት ሀሰን አል በሽር ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።የረጅም ጊዜ ግንኙነት ያላቸው ኢትዮጵያ እና ሱዳን በንግድ እና ኢንቨስትመንት እንዲሁም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።ሁለቱ ሀገራት ድንበር ተሻጋሪ የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳደግም ተስማምተዋል-(ኤፍ.ቢ.ሲ) ፡፡", "passage_id": "9602d8114d542fe4cd68c18d9cfc2b8a" }, { "passage": "የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ከተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሃገር ውስጥ ሚኒስትር ሌተናንት ጄነራል ሼክ ሰይፍ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ተወያይተዋል።\nሁለቱ ሃገራት ያላቸው የትብብር መስኮች በተለይም በማህበረሰብ አቀፍ ፖሊሲ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያላቸው ትብብር የውይይታቸው ማጠንጠኛ ነው፡፡\nበውይይቱ ላይ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ ሌሎች የፌደራል ፖሊስ የስራ ኃላፊዎችም ተገኝተዋል።\nበተያያዘም የሰላም ሚኒስትሯ ከአቡ ዳቢ ልማት ፈንድ ጄኔራል ዳይሬክተር ሞሃመድ ሰይፍ አል ሱዌይዲ ጋር ውይይት አድርገዋል።\nበውይይታቸው ወቅትም በኢትዮጵያ የልማት ፕሮጀክቶችን መደገፍ እና የኢንቨስትመንት አማራጮችን መለየት በሚቻልበት ጉዳይ ላይ መክረዋል።\nየልማት ፈንዱ እና የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬትስ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማት ለሚያደርጉት ድጋፍ የሰላም ሚኒስትሯ ምስጋና አቅርበዋል።\nአያይዘውም የልማት ፈንዱ በተለያዩ የዓለም ሃገራት ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ዘርፎች ለሚያደርገው ድጋፍ ያላቸውን አድናቆትም ገልጸዋል።\nጄኔራል ዳይሬክተሩ በበኩላቸው ፈንዱ በታዳጊ ሃገራት በተለይም በአፍሪካ የሚያደርገውን የልማት እንቅስቃሴ የማስፋት ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል፡፡\nፈንዱ በአፍሪካ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች የመንግስታቱን ድርጅት ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት የሚደረገውን ጥረት በሚደግፍ መልኩ ውጤት እያመጡ መሆኑን አስረድተዋል።\nየሚኒስትሯ ጉብኝት በኢትዮጵያ መንግስትና በልማት ፈንዱ መካከል ያለው ግንኙነት እንዲጠናከር እና ኢንቨስትመንትን ማስፋፋት በሚቻልበት አግባብ ላይ ለመምከር የሚያስችል እድል እንደፈጠረም ገልጸዋል፡፡\nየአቡ ዳቢ ልማት ፈንድ ከፈረንጆቹ 2012 ጀምሮ በኢትዮጵያ ከ32.5 ሚሊየን ዶላር በላይ ለሚያወጡ 2 የልማት ፕሮጀክቶች ድጋፍ አድርጓል።\n\nምንጭ፡- ኤሚሬትስ የዜና አገልግሎት\n", "passage_id": "c0ee16c186add0207a5def2f397af642" }, { "passage": "ፕሬዚዳንቱ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር በሁለትዮሽና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።የፕሬዚዳንት ሞሐመድ ዐብዱላሂ ጉብኝት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በአፍሪካ ቀንድ ሰላም ለማስፈንና የኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር የጀመሩት ዲፕሎማሲያዊ እንቅሰቃሴ አካል ነው ተብሏል።", "passage_id": "32352ac6119d05600dd23466b90dd813" }, { "passage": "በአዲስ አበባ እየተካሄደ ከሚገኘው 30ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ጎን ለጎን ስብሰባ ያደረጉት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አካባቢው ተደማጭነቱ እንዲጎለብት ለመስራት ተስማምተዋል፡፡የቀጠናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ምክክር አካባቢያዊ ተሰሚነት እንዲጎለብትና ሰላምና መረጋጋት በሚሰፍንበት ጉዳይ ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡፡የአፍሪካ ህብረት ቀጣይ ሊቀመንበር የሆነችውን ሩዋንዳ እንዲሁም የአፍሪካ ህብረትን ተቋማዊ ለውጥ በበላይነት እያንቀሳቀሱት ያሉትን የሀገሪቱን ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜን በሚኖራቸው የስራ ቆይታ ለመደገፍ መስማማታቸውን ምክክሩን የተከታተሉት የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሀሙድ አሊ ዩሱፍ ገልፀዋል፡፡በውይይቱ ቀጠናዊ የኢኮኖሚ ትብብር በሚጠናከርበት ሂደት ላይ ሚኒስትሮቹ መስማማታቸውም ተጠቅሷል፡፡በውይይቱ የአስራ አራት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን የኮሞሮስና የሶማሊያ አዲስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችም ትውውቅ ተካሂዷል፡፡ ", "passage_id": "6a00f78441a197b3f06363cbb9627ea1" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ታህሳስ 11፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከሱዳኑ አቻቸው አብደላ ሓምዶክና ከሶማሊያው ፕሬዚዳንት መሀመድ ፋርማጆ ጋር የተናጠል ውይይት አካሄዱ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ  ከሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሓምዶክ ጋር በጋራ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል።መሪዎቹ በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል።መሪዎቹ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከርና አካባቢያዊ ትስስርን ማጎልበት ላይ ተወያይተዋል።በተመሳሳይ  ከፕሬዚዳንት መሀመድ ፋርማጆ ጋር የኢጋድ አባል ሀገራትን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር መሰራት እንዳለበት መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በትዊተር ገጿቸው ገልጸዋል።እንዲሁም  ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ከ38ኛ የኢጋድ አስቸኳይ የመሪዎች ስብሰባ ጎን ለጎን የሁለትዮሽ ውይይት አካሄደዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣናዊ እና በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ከፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር መምከራቸውን ገልፀዋል።ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችን ያካተተ የልኡካን ቡድን ወደ ስፍራው አቅንቷል።ጉባኤው በአፍሪካ ቀንድ የሰላምና ፀጥታ እንዲሁም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ዙሪያ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!", "passage_id": "dfe7e337df387049a4e5eeb4af39ca1d" } ]
703378c7cc1476fc27f936bb100bde37
e93f4d4335bdcf01af96a4fc8f261570
አድሏዊ የመገናኛ ብዙኃን ዘገባ የህዝብን ጥላቻን በማባባስ የአገር አደጋ እየሆነ መምጣቱ ተገለጸ
ጽጌረዳ ጫንያለው አዲስ አበባ፡- የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች በከፍተኛ ሁኔታ አድሏዊነት እየታየባቸው በመምጣታቸው ጥላቻን በማባባስ የአገር አደጋ እየሆነ መምጣቱን አስተያየታቸውን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ የሰጡ የዘርፉ ምሑራን ተናገሩ። በውጪ ሚዲያዎች የሚታየው የአድሎ ዘገባ ምንጩ ችግሩን ከምንጩ አለመረዳት እና ችግሩ ያደረሰውን እንጂ ያመጣውን ማየት አለመፈለጋቸው መሆኑንም ገልጸዋል።በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት መምህር ዶክተር ሙላቱ አለማየሁ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ መገናኛ ብዙኃን የህዝብ ልሳን በመሆናቸው የሁሉንም ሀሳብ በእኩል ደረጃ ማስተናገድ ቢኖርባቸውም ይሄን እያደረጉት እንዳልሆነ በተለያየ መንገድ ይታያል። በዚህም ግለሰቦችን ለማጉላት ሲሞክሩ፤ የአንድ ወገን ሀሳብ ብቻ ሲያስተናግዱ፤ ከጋዜጠኛው ጀርባ ያሉ አካላት ፍላጎትን ሲያሳኩም ይስተዋላል። ይህ ደግሞ በህዝብ መካከል ጥላቻን በማባባስ አገርን አደጋ ውስጥ እንድትገባ እያደረጋት ይገኛል። በመገናኛ ብዙኃኑ ዘገባዎች የጋዜጠኛው ፍላጎት፣ የአገራት ፍላጎት፣ የፖለቲካና የሚፈለገው የርዕዮተዓለም ፍላጎት እንዲሁም የብሔር ፍላጎት ሰፊውን ድርሻ ወስዶ በመዘገቡ የህዝብን ሀሳብ እየታፈነ እንደሆነ ይታያል የሚሉት ዶክተር ሙላቱ፤ መገናኛ ብዙኃኑ የህዝብ አገልጋይነታቸውን መልቀቃቸውን እና ሀሳቦች እንዳይንሸራሸሩም ወገንተኝነታቸው መብዛቱን ይገልጻሉ። በተለይም የክልል ሚዲያዎች በዚህ ዙሪያ ከፍተኛውን ድርሻ እየወሰዱ መሆኑን፤ ይህ ደግሞ በህዝብ መካከል ጥላቻና ቂም እንዲፈጠር እድል መስጠቱን፤ ሂደቱም አማራጭ የመፍትሄ ሀሳቦች እንዳይኖሩም እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል። የዜጎች ድምጽ መታፈንን ከሚያመላክቱ መንገዶች አንዱ አድሏዊ ዘገባ እንደሆነ የሚጠቁሙት ዶክተር ሙላቱ፤ ሀሳብ ሳይወጣ ሲቀር ፍርሀትና ስጋት ይፈጥራል። ይህ ደግሞ ቂም አርግዞ ለቀጣይ ጊዜ ከፍተኛ ችግር በህዝቦች መካከል እንዲከሰት ያደርጋል። የተረጋጋ ህይወት ለመኖርም አያስችልም። ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን ልዩነት በትክክል እንዳያዩ ያደርጋቸዋል። ስለዚህም አሁን በጥናት ባይረጋገጥም አገሪቱ ላይ እየሆነ ያለው ይሄው መሆኑን ተናግረዋል። ወቅቱ ብዙ ችግሮችን አርግዞ የቆየበት በመሆኑ የአገር ውስጥ ሚዲያዎች በተለይም የክልል መገናኛ ብዙኃን ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው የሚናገሩት ዶክተር ሙላቱ፤ ተጎጂውም ሆነ ጎጂው የአንድ አገር ዜጋ በመሆኑ መገናኛ ብዙኃን ሁለቱንም ማዕከል ያደረገና ግራ ቀኙን ያየ ዘገባ ማዘጋጀት እንዳለባቸው አስረድተዋል። የሰላም ግንባታ ላይ መስራት ሚዲያው ለቆመለት አላማ ከመታመንም በላይ ህዝብንና አገርን ከችግር መታደግ ነው። ስለሆነም መገናኛ ብዙኃኑ ዘገባቸውን እንደ መከላከያ ለህዝብና ለሰላም ወገንተኝነትን መሰረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። ለዚህ ደግሞ አድሏዊነትን ትተው ሚዛናዊነትን ማስቀደም እንደሚገባቸውም ገልጸዋል። እንደ ዶክተር ሙላቱ ገላጻ፤ በውጪ ሚዲያዎች የሚታየው የአድሎ ዘገባ ምንጩ የተለያየ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ችግሩን ከምንጩ አለመረዳት ነው። ሌላው ችግሩ ያደረሰውን እንጂ ያመጣውን ማየት አለመፈለጋቸው ነው። ነገሮችን ተከታትሎ አለመዘገብ፣ የራሳቸውን ፍላጎት ማስቀደምም፣ ሌላው የአድሎአዊነት መሰረታቸው ነው። ስለሆነም በአገር ውስጥም ሆነ በውጪ የሚገኙ አድሎአዊ ዘገባዎችን ለማስቀረት ከራስ የጀመረ ሥራ ያስፈልጋል። እንደ ሚዲያ ያለውን ህግ መሰረት አድርጎ ግራ ቀኝ አይቶ መዘገብ ደግሞ የመጀመሪያ መፍትሄ ነው። መረጃ የሚሰጡ አካላት ትክክለኛውን መረጃ ወቅቱን በጠበቀ መልኩ ሊሰጡ እንደሚገባ የጠቆሙት ዶክተር ሙላቱ፤ በተለይም ለውጪ ሚዲያዎች በየቀኑ መግለጫ መስጠትና እውነታውን ማሳየት እንደሚገባ አስረድተዋል። በተመሳሳይ በኢንባሲዎች አካባቢ ሥራዎች መሰራት ያስፈልጋል። እንደመንግሥት ጋዜጠኞችን ወቅታዊ ጉዳይ ባለበት ስፍራ ይዞ በመጓዝም እውነታውን ማሳየት ተቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት ብለዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን መምህር እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪ ተማሪው መምህር ፍሬዘር እጅጉ በበኩላቸው እንደሚናገሩት፤ ከለውጡ በኋላ በተሰጠው የሚዲያ ነጻነት ጥናት ተደርጎ እንደተገኘው በአገሪቱ ያሉ የሚዲያ ተቋማት ዘገባ ከፍተኛ አድሏዊነት የሚታይበት ነው። የአንድ ወገንን ሥራ የሚያጎላም ነው። ይህ ደግሞ ቀጣይነት ያለው ችግር እንደሚፈጥር የታየበት ሲሆን፤ አሁን የተፈጠረውም ከዚሁ ግምት ጋር ይያያዛል።ከውጪ ሚዲያ አንጻር ሲታይ ደግሞ አፍሪካ በዓለም መገናኛ ብዙኃን የምትወከለው የጦርነት ምድርና የችግር ምሳሌ በመሆን ስለሆነ በፊት ገጻቸው ከዚህ የተለየ ማስፈርን እንዳይችሉ አድርጓቸዋል። ምክንያቱም የውጪ ሚዲያዎች በአፍሪካ ያለውን ሰላም፣ ስኬትና ልማት የሚያዩበት መነጽር የተሳሳተ ስለሚሆን ለተነባቢነታቸው ስለሚጨነቁ መዘገብ አይፈልጉም።እንደነዚህ አይነት ችግሮችን ለመፍታት ሁለት መንገዶችን መጠቀም እንደሚበጅ የሚናገሩት መምህር ፍሬዘር፤ በውጪዎች እይታ የሚደማ ነገር ካለና መጥፎ ዜና ከሆነ ጥሩ ዜና ተብሎ ፊት ገጽ እንዲሆን ይፈቀዳልና ይህንን ባህሪያቸውን አቅርቦ በጥሩ መቀየር እንደሚገባ ይገልጻሉ። ለዚህ ደግሞ አሁን በወቅታዊ ጉዳዮች እንደተቋቋመው የመረጃ ፍሰት ማዕከል አቋቁሞ ከፍተኛ የህዝብ ግንኙነት ስትራቴጂን መፍጠር ትልቅ ውጤት እንደሚያስገኝ ተናግረዋል። የአገር ውስጥ ሚዲያው መፍትሄ ደግሞ፣ ህዝብን ለውዥንብርና ብዥታ የሚዳርጉ ሚዲያዎችን ብሮድካስት እርምጃ እየወሰደ ማስተካከል እንደሚገባ በመጠቆም፤ ሚዲያው በራሱ የተለያየ ሀሳብ ያላቸውን ሰዎች በመጋበዝ ሚዲያው የሀሳብ ማንሸራሸሪያ መድረክ እንዲሆን መስራት ይኖርባቸዋልም ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37769
[ { "passage": "በማህበራዊ ድረገፆች ጥላቻን የሚዘሩ ንግግሮች በመሰራጨታቸው አገር እንዳትረጋጋ እያደረጉ ነው። ጉዳዩ ያሳሰባቸው የዘርፉ ባለሙያዎች ማህበራዊ ድረገፆች የአጠቃቀም ገደብ ይበጅላቸው ይላሉ። ጉዳዩን አጥንቶ መፍትሄ የሚሰጥ አካል እንደሚያስፈልግም ይገልጻሉ።ዶክተር ደምመላሽ መንግስቱ በጅማ ዩኒቨርስቲ ፐብሊክ ሪሌሽን ኤንድ ኮሙኒኬሽን ኢን ዘካልቸራል ኮሙኒኬሽን ረዳት ፕሮፌሰር ናቸው። የጥላቻ ንግግሮች መንስኤ የቋንቋና ተግባቦት ተጣጥመው ያለመገኘታቸው ውጤት ነው። በተለይ ቋንቋ ከሚሰጠው ተግባር አኳያ በተለያየ መንገድ መተርጎም መቻሉ የጥላቻ መልክ ይዘው የሚወጡ ንግግሮች እንዲበዙ እያደረጉ ነው። ይህ አካሄድ ደግሞ ለአገር ህልውና እጅግ ከባድ መሆኑን ይናገራሉ።ማህበረሰቡ ንግግሮቹን የሚፈታው ባለው አቅም ልክ ስለሆነ ግለሰብ የሚፈልገውና የራሱ የሆነውን ስሜት ሲጽፍ ቡድናዊ ይሆናል። በተሳሳተ መንገድ የተረዳቸውን ሀሳቦች ማጋራቶችና መውደዶች ይበዙና ጥላቻ እንዲስፋፋ እድል ይፈጠራል። ከፖለቲካው ትኩሳት የተላቀቁ መገናኛ ብዙሃን ባለመኖራቸው የጥላቻ ንግግሮች በማህበራዊ ድረገጾች የሚራገቡበትን እድል እንደፈጠረ ይናገራሉ።በባህርዳር ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለምአቀፍ ጥናት መምህሩ አቶ እምቢአለ በየነ፤ ማህበራዊ ድረገጾች ማህበረሰቡ የቡድንም ሆነ የግል አመለካከቶችን የሚያንጸባርቅባቸው አማራጮቹ ናቸው። አሁን ባለው ሁኔታ በቡድን የሚዘሩ የጥላቻ ንግግሮች በርካታ የመሆናቸውም ምስጢርም ይኸው ነው ይላሉ። በተለይ የብሔር ጥላቻን የፈጠሩ ማህበራዊ ድረገፆች ያለገደብ በነጻነት ስለሚሰራባቸው እንደሆነም ያብራራሉ።ማህበራዊ ድረገፆች አገር እንዳትረጋጋ፣ ሰዎች እንዲፈናቀሉና እርስ በእርስ እንዲገዳደሉ ብሎም ብሔር በብሔር ላይ እንዲዘምትና የመግባባት እድሎች እንዲጠቡ ያደረጉት ዋናው ምክንያት በአግባቡ የመጠቀም ልምድ አናሳ በመሆኑ ነው። በተጨማሪም የማህበራዊ ድረገፆች የአጠቃቀም ህግ አለመኖሩና ብዙ ሰው በሚታወቅበት ስሙና ፎቶው ባለመጠቀሙ የጥላቻ ንግግሮች እንዲበራከት በር ከፍቷል። ተጠቃሚዎች ተጠያቂነት ባለው መልኩ ማህበራዊ ድረገፆችን እንዲገለገሉበት ባለመደረጉ ችግሩን እንዳገዘፈው ያስረዳሉ።‹‹የጥላቻ ንግግር ከዚህ በተለየ መልኩ መታየት አለበት» ይላሉ። ባልሆነ ወይም ባልተሰራ ነገር ላይ መናገር፣ በቡድን የሚከፋፈሉና ብሔር ተኮር የሆኑ ንግግሮችን መጻፍና መለጠፍ የጥላቻ ንግግሮች መገለጫ ናቸውና ጥላቻን ከትክክለኛው ንግግር ለመለየት ማስቸገሩ በአገር ላይ ትልቅ አደጋ እየጣለ የመጣ ጉዳይ መሆኑንም ያነሳሉ።እንደ አቶ እምቢአለ ማብራሪያ፤ በህጋዊ መንገድ ተቋቁመው የሚሰሩት መገናኛ ብዙኃን ከማህበራዊው ሚዲያ ቀድመው መረጃዎችን ማስተላለፍ አለመቻላቸው ለጥላቻ ንግግሮች መስፋት ምክንያት ሆነዋል። መደበኛው የመገናኛ ብዙሃን የማህበራዊ ድረገጾች ሲያራግቡት የቆዩትን መረጃ እንደ አዲስ ደግመው ይሰሩታል። ይህ ደግሞ ተአማኒነትን ያሳጣል። በዚህም ታማኝ ምንጮች ማህበራዊ ድረገጾች ይሆኑና የተሳሳቱና ጥላቻን የሚዘሩ ንግግሮች እንዲስፋፉና ተመራጭ እንዲሆኑ ምክንያት ይሆናል።በኮተቤ ሜትሮፖሊታል ዩኒቨርሲቲ የህግ አገልግሎት ዳይሬክተርና የፕሬዚዳንቱ ልዩ አማካሪ ዶክተር ተስፋዬ ባዬ በበኩላቸው፤ በማህበራዊ ድረገጾች የሚለቀቁ የጥላቻ ንግግሮች ምንጫቸው የተጠና ባይሆንም በተማረው ኃይል ላይ በስፋት እንደሚስተዋሉ ታዝበዋል። ይህ ደግሞ ወደ አልተማረው የህብረተሰብ ክፍል ይተላለፍና የተሳሳተ አመለካከትን እያራገበ የብሄር ግጭትን ያስፋፋዋል። የመረጃ ምንጮቻቸው ታማኝ እንደሆኑ በማሰብም የአገሪቱን ህዝቦች የመግባባትና የመስማማት እድላቸውን ያጠበዋል ይላሉ።«የፍራቻ፣ የጥላቻና መሰል ጉዳዮች ግፊት የጥላቻ ንግግር መገለጫ ናቸው» የሚሉት ዶክተር ተስፋዬ፤ ፖለቲካው በወለደው ችግር ምክንያት በአሁኑ ወቅት አገሪቱ በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ መስማማት እንዳትችል እያደረጋት ነው። እውነትና ውሸቱን በሚገባ ለይቶ መገንዘብ የሚችል ማህበረሰብ ገና አልተገነባም። በመሆኑም ትንሽ እውነታ ይዞ ግነት የታከለበት ውሸትም እያናወጣት ነው።እንደ ዶክተር ተስፋዬ ገለጻ፤ አሁን በማህበራዊ ድረገፆች ላይ የጥላቻ ንግግሮች ውድድር ውስጥ ገብተዋል። ማሸነፍና መሸነፍ የማይታይበት ነውና ማህበረሰቡ የማይወጣው ችግር ውስጥ እየገባ እንዲሄድ አድርጎታል። ሌላ አገር ላይ የተከሰተን ጉዳይ ሳይቀር በፎቶ እያቀናበሩ ማቅረብ ተጀምሯል። ይህ ደግሞ አገር በሰብአዊነት ጭምር እንድትፈተንና የበለጠ ግጭት ውስጥ እንድትገባ እያደረጋት ይገኛል።በተለይ በዩኒቨርስቲዎች ደረጃ የጥላቻ ንግግሮች ገነው ስለሚወጡ አንድ ዩኒቨርስቲ ምንም ችግር ሳይፈጠር ሌላው ጋር «የእገሌ ብሔር ተወላጅ ተገደለ» በሚል እርስ በእርስ እንዲጋጩ እየተደረገ ነው። ይህ አካሄድ አገሪቱ ውስጥ ተማሪዎች ተረጋግተው መማር እንዳይችሉ አድርጓል።አገሪቱ በሁሉም ነገር ገና በማደግ ላይ ያለች ከመሆኗ ጋር ተያይዞ ቴክኖሎጂ በአግባቡ የመጠቀም ችግሮች ይስተዋላሉ። በመሆኑም መፍትሄው ህግ አውጥቶ ተጠያቂነት የሚሰፍንበትን አሰራር በመፍጠር እንደሆነ ዶክተር ደምመላሽ ይናገራሉ። በዚህ ሀሳብ የሚስማሙት ዶክተር ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ማህበራዊ ሚዲያው ከመደበኛው ኢንተርኔት ውጪ ተዘግተው ለተወሰነ ጊዜ የግንዛቤ ማስጨበጥ ተግባር ቢከናወን የጥላቻ ንግግሩም ሆነ በአገር ላይ እየተፈጠረ ያለው ችግር መፍትሄ ያገኛል ይላሉ። በተመሳሳይ መምህር እምቢአለም መደበኛውና ተጠያቂነት ያለበት መገናኛ ብዙሃን ከማህበራዊ ሚዲያዎች ቀድሞ መረጃ የሚያደርሰበትን አሰራር መዘርጋት እንደሚገባ ይናገራሉ።በቅርብ ጊዜ የወጣ መረጃ እንደሚያመላክተው በሀገራችን16ነጥብ4 ሚሊዮን የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ይገኛሉ። 3ነጥብ6ሚሊየን የሚሆኑት የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ናቸው። በማይናማር፣ በኬኒያ፣ በደቡብ አፍሪካና በደቡብ ሱዳን በነበሩት ቀውሶች በማህበራዊ ሚዲያው የተቀነባበሩ እንደነበሩም መረጃዎች ያመላክታሉ።የጥላቻ ንግግሮቹ ገደብ ካልተበጀላቸውና በዚህ ከቀጠሉ ሰብዓዊ መብት ማክበር አይኖርም፤ ብሔር ከብሔር ጋር የመጋጨቱ ሁኔታ ይሰፋል፤ በአገሪቱ ላይ ሰላምና መረጋጋት ይጠፋል።በአጠቃላይ አገሪቱ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ትገባለች።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2011\nበጽጌረዳ ጫንያለው", "passage_id": "577ac3f45b8fede3abe8e3bf3a30c48d" }, { "passage": "ባለንበት ዘመን ማኅበራዊው የመገናኛ መድረክን ጨምሮ የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ስፍር ቁጥር የሌለውን መረጃ በየደቂቃው ለታዳሚዎቻቸው ያቀርባሉ።ዘነበ (ዶ/ር)፡ቢቢሲ፡ ከዚህ በፊት በነበረው የኢህአዴግ ሥርዓት፡ ሚድያው የመንግሥት አፈቀላጤ ሆነ ተብሎ ሲተች ነበርና፣ አሁን በዚህ ሁለትና ሦስት ዓመታት ውስጥ በሚድያው ላይ ምን ለውጥ ተመለከቱ? ዘነበ (ዶ/ር)፡ቢቢሲ፡ የመገናኛ ብዙሃን ሁኔታ በዚህ ከቀጠለ ምን ሊያስከትል ይችላል ይላሉ?ዘነበ (ዶ/ር)፡ቢቢሲ፡ አሁን በተጨባጭ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ካነሱዋቸው ችግሮች ኣንጻር ምን ይደርግ ይላሉ?ዘነበ (ዶ/ር)፡በዚህ ሂደት ውስጥ ጠቃሚና ሐቀኛ መረጃዎች የመቅረባቸውን ያህል አሳሳችና አደገኛ ወሬዎች ተሰራጭተው አለመግባባትና ጉዳትን ያስከትላሉ።በተለይ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ቁጥራቸው የበዛ የተለያየ አላማ ያላቸው የመገናኛ ብዙሃን ወደ ሕዝቡ እየደረሱ ባሉበት ጊዜ ስጋት የሚፈጥሩባቸው አጋጣሚዎች ጥቂት የሚባል አይደለም።ከዚህ አንጻር የታዘቡትንና መደረግ አለበት የሚሉትን እንዲያካፍሉን ዘነበ በየነን (ዶ/ር) ጋብዘናል።ዘነበ በየነ (ዶ/ር) አሜሪካ በሚገኘው የሚሲሲፒ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት ትምህርት መምህር ናቸው። በአብዛኛው ጥናቶቻቸው መገናኛ ብዙኀን ለሰላምና ለአገር ግንባታ ያላቸውን አስተዋጽኦን ይመለከታል። በቅርቡ ደግሞ፤ 'ሁሉ የሚያወራበት፤ አድማጭ የሌለበት' የሚለው ጥናታቸው በተለይ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ አለ የሚሉትን ነባራዊ ሁኔታን እንደሚገልጽላቸው ይናገራሉ። መገናኛ ብዙኀን የሚጠበቅባቸውን ከወገንተኝነት በራቀ ሁኔታ ሙያዊ በሆነ መልኩ የሚሰሩ ከሆነ በሕዝብ መካከል መግባባትን ለመፍጠር የመቻላቸውን ያህል በተቃራኒው ከሆኑ ደግሞ አለመግባባትና የሠላም መናጋትን ሊያስከትሉ ይችላሉ።ከዚህ አንጻር ቢቢሲ ለ ዘነበ (ዶክተር) የሕዝብን ሰላም ሊያናጉ የሚችሉ ዘገባዎች የሚሉዋቸው የትኞቹ እንደሆኑና ሕዝቡ ሐሰተኛውን ከሐቀኛ ዘገባ እንዴት ነው መለየት ይችላል? ለሚለው ጥያቄ መልስ በመስጠት ይጀምራሉ፡ ብዙ ነው። ሌላ አካባቢ የተደረጉ ነገሮችን ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ተደረገ አድርጎ ማቅረብ ኃላፊነት የጎደለው ነው። ከሁሉ በላይ ለአንድ ሚድያ ትልቁ ዋጋው እምነት ነው። አንድን ነገር ሲፈጸም አንዳንድ ሚድያዎች \"የሆነው ነገር ምንድን ነው፤ መረጃ ከየት ነው የምናገኘው? ያገኘነው እንዴት ነው የምንጠቀምበት?\" ብለው ሊያስቡበት ይገባል። የሕብረተሰቡን ንቃተ ህሊና መጨመር ያስፈልጋል። ሕዝቡ፣ ውሸት የሚነዙ ሚድያዎችን እርግፍ አድርጎ የሚተዋቸው፤ ንቃተ ህሊናው ከፍ ያለ እንደሆነ ብቻ ነው።የዛሬ ሦስት ዓመት የተደረጉትን ዛሬ እንደተደረጉ አድርጎ ማቅረብ ከማንም በላይ የሚጎዳው ራሱ ሚድያውን ነው። ለጊዜው ሕዝብን ሊያደናግር ይችላል፤ ከሁሉም በላይ ግን ራሱ ሚድያው ነው ተዓማኒነቱን የሚሸረሸረው። መንግሥት፤ እንደዚህ ዓይነት ኃላፊነት የጎደላቸው የሚድያ አውታሮችን ተጠያቂ ሊያደርግ ይገባል። ያ ሚድያ መንግሥታዊ ሊሆን ይችላል የግል ሊሆን ይችላል። ምንም ለውጥ የለውም። ኃላፊነት የጎደለው ሥራ እስከሰራ ድረስ፣ መጠየቅ የመንግሥት ግዴታ ነው። መንግሥት የሕዝብን ደኅንነት የመጠበቅ ግዴታ አለበት። ይህ ተደጋግሞ ሲነሳ እሰማለሁ። \"መንግሥት ተለውጧል፤ ሚድያውስ ለውጧል ወይ?\" የሚል። አንድ ደረጃ ወደ ኋላ መሄድ ያለብን ይመስለኛል። ኢትዮጵያ ውስጥ መንግሥት ተቀይሯል ወይ? ሁላችንም ጥያቄ አለን። ምክንያቱም እርግጥ ነው አስተዳደሩ ተቀይሯል። ከአቶ መለስ ወደ አቶ ኃይለማርያም፤ ከአቶ ኃይለማርያም ወደ ዶክተር ዐብይ የስልጣን ሽግግር ተደርጓል። መዘንጋት የሌለብን ግን ሁሉም ኢህአዴጎች መሆናቸውን ነው። በዶ/ር ዐብይ ጊዜ ብዙ ልናስባቸው የማንችላቸው አንዳንድ ለውጦችን እየተመለከትን ነው። እሱ ላይ ጥርጣሬ የለኝም። 'ከዚያው አንጻር ሚድያው ተቀይሯል ወይ?' የሚለው ጥያቄ ግን ልንመረምረው የሚገባ ጉዳይ ይመስለኛል። ምክንያቱም፣ ጋዜጠኞቹ እነዚያው ናቸው፣ መሰረተ ልማቱ ያው ነው። አስተሳሰቡ [ማይንድ ሴቱ] ያው ነው። ከሁሉም በላይ የፖለቲካ ባህል የምንለው ያው ነው። ጋዜጠኛው የኅብረተሰቡ ውጤት ነው። ኅብረተሰቡ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ባህል ተቀይሯል ወይ? ብለን በምናስብበት ሰዓት እንደውም ጥግ የመያዝ ሁኔታ አሁን የባሰ እየጎላ የመጣ ይመስለናል። ምክንያቱም አንዳንድ ሚድያዎች በተለይ ደግሞ ሶሻል ሚድያው ላይ፤ ጥግ ይዞ ድንጋይ መወራወር ላይ ነው ያለው። ያ ድንጋይ የሚወረወረው ግን ሕዝብ ላይ ነው፤ ወገን ላይ ነው። አገር ላይ ነው። አንዳንዴ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን መሆናችን የረሳን ይመስለኛል።ምንድነው እያደረገን ያለነው? እየሄድን ያለነው ወዴት ነው? የሚለውን ነገር በአግባቡ ልንመለከተው ይገባል። ቀደም ሲል እንዳልኩት፤ የመንግሥት አስዳደር ለውጥ የፖለቲካ ባህሉና ባህሪው እስካልቀየረው ድረስ ያ በድሮ 'ማይንድ ሴት' ውስጥ ያለው ሚድያ አዲስ ነገር ያመነጫል ብሎ መጠበቅ በጣም ከባድ ነው። ከሁሉ በላይ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ አስቸጋሪ የሚያደርገው ሁኔታ ሁሉም በየአካባቢው ሶሻል ሚድያ አለው፤ ወይም ደግሞ ጠንካራ የሆነ የራሱ ሚድያ አለው። ስም መጥቀስ አያስፈልግም። ሁላችንም የምናውቃቸው ናቸው። በነገራችን ላይ ሚድያው ዛሬ በአግባቡ ካልተገራ ነገ ዋጋ ያስከፍለናል። ምሳሌ ለመጥቀስ ኬንያ በ2007/8 (እኤአ) ከምርጫው በኋላ የተከሰተው ግጭት በአብዛኛው እሳት ያቀጣጥሉ የነበሩት፤ ለግጭቱ ከፍተኛ አስተዋጸኦ ሲያደርጉ የነበሩት የሬድዮ ጣብያዎች ናቸው። ለምሳሌ ሪፍት ቫሊ አካባቢ የነበረው የሬድዮ ጣብያ ትልቁን ሚና ተጫውቷል። አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ነባራዊ ሁኔታም መንግሥት አስፈላጊውን ትኩረት ሰጥቶ ሚድያዎቹን ማስተካከል ካልቻለ ነገ ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍሉናል። ስለዚህ \"የመንግሥት ለውጥ ተደርጓል፤ ሃሌ ሉያ ስለዚህ የሚድያ ለውጥ ይኖራል፤ ወደ ተስፋይቱ ምድር እየገሰገስን ነው፤ ነገሮች ሁሉ አልጋ በአልጋ ሆነዋል\" ብለን የምናስብ ከሆነ ራሳችንን እያታለልን ነው። ከሁሉ በላይ ሶሻል ሚድያው እየፈጠረው ያለው አደጋ ቀላል አይደለም። ሚድያው አንዳንድ ጊዜ የሚሰነዝራቸው ነገሮች ለሶሻል ሚድያ መልስ የመስጠት እስከሚመስል ድረስ ነው። ማይንማር [በርማ] የተፈጠረው ከፍተኛ ዘር ተኮር ጥቃት [ዘር ማጥፋት] በማኅበራዊ ሚድያው ዋና መሪነት የተካሄደ መሆኑን ልናውቅ ይገባል። እኛ አካባቢስ ሚድያዎቻችን ምን እየሰሩ ነው ያሉት ብሎ መመርመር ያስፈልጋል። በሌሎች ሚድያዎች የማየው ነገር ችግሩ እንዳለ ነው። አፈቀላጤ የመሆን፣ ኃላፊዎችን የመፍራት፣ በአንድ አቅጣጫ የመሄድ ነገር ይታያል። ከዚያ በዘለለ የሕዝቡ የልቡ ትርታ ማደመጥና ብዙ ሥራ መስራት የሚጠበቅብን ይመስለኛል። ይህንን ስል በፌዴራል ላይ ያሉትንም በክልል ላይ ያሉትንም ይመለከታል። ሚድያው ውስጥ ያሉት ሰዎች መሆናቸው አንዘንጋ። በተለያዩ ምክንያቶች ስህተት ይሰራሉ። 'ኢትዮጵያ ውስጥ እንዴት ብቁ ጋዜጠኛ መፍጠር እንችላለን?' ብለን ማሰብ አለብን። ሕንድ ለምሳሌ ትልቁ የዲሞክራሲ አገር እየተባለች የምትንቆለጳጰሰው ጥሩ የሚባል ሚድያ ስላላት ነው። ጋና፣ ኬንያና ደቡብ አፍሪካ እነዚህ ሚድያዎች ከሌላ ጋር ሲነጻጸር ውጤታማ የሆነ ዲሞክራሲ እንዲፈጠር የራሳቸው ሚና ተጫውተዋል። ኢትዮጵያም ውስጥ የምንፈልገው ዲሞክራሲና የሰብዓዊ መብት አያየዝ እንዲመጣ ከፈለግን የሚድያው ሁኔታው መለወጥ አለብን። ማብቃት አለብን። መጀመሪያ ነገር ሁልጊዜ በተደጋጋሚ ስልጠናዎች መስጠት ይገባል። ለምሳሌ በእርድ ሥራ ላይ የተሰማራ ሰው ቢላውን አስር ግዜ መሞረድ አለበት፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ መስራት ስለሚያቆም። ብዙ ነገሮች ስለሚለዋወጡ ሚድያውም እንደዚያ ነው። ጋዜጠኞች አቅማቸውን የምንገነባ ከሆነ አስፈላጊውን ግብዓት የምናቀርብላቸው ከሆነ የማይቀየሩበት ምክንያት የለም። ይሄ ሁሉ ተደርጎ የማይቀየሩ ካሉ፤ ኬንያ ውስጥ አንድ የሚታወቁበት ነገር አላቸው። 'ኔሚንግ ኤንድ ሼሚንግ' [መጥፎ ድርጊትን ማጋለጥ] ይሉታል። ጋዜጠኞች ሆኑ ፖለቲከኞች ኃላፊነት የጎደለው ሥራ በሚሰሩበት ጊዜ፣ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት በሚሞክሩበት ጊዜ እንዲሸፈኑና እንዲደበቁ አይፈቅዱላቸውም። አሜሪካ በምትመጣበት ጊዜ ሲቪክ ማኅበረሰቦች አሉ፤ ዘረኝነትን የሚሰብክ የሚድያ አውታሮችን 'ኔሚንግ ኤንድ ሼሚንግ' የሚለው ዘዴ እየተከተሉ ይሰራሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንደዚህ ካልተደረገ በስተቀር፤ የእኔን ፍላጎት ስለአንጸባረቀልኝ ብቻ ይሄኛው ሚድያ ትክክል ነው የምል ከሆነ፤ ልክ አይደለም።ዛሬ ምናልባት ሴቶችን ብቻ ለይቶ የሚያጠቃ ሚድያ ካለ፣ 'እኔ ወንድ ነኝ፤ አይመለከተኝም' ብለን የምናልፈው ከሆነ፤ ነገ እኔጋ ሲመጣ ሊያስቆመው የሚችል ኃይል አይኖርም። ስለዚህ በአንድ ወገናችን ላይ የሚሰራው የሚድያ ጥቃትና ግፍ ሁላችንም ላይ እንደተሰራ አድርገን ልንቆጥረው ይገባል። ስለ እውነትና ስለልጆቻችን ስንል ሚዲያው ዛሬ በአግባቡ ካልተገራ ነገ ከባድ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል። ", "passage_id": "6bbd4d8894aef4aa340d3eda181da2b1" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ መስከረም 23/2012 ዓ/ም (አብመድ) የዘገባ የይዘት ምንጭን ከአንድ ወገን ብቻ በማድረግና የዘገባ ትክክለኝነትን በመጣስ በሕዝቦች መካከል የእርስ በርስ ግጭት በመቀስቀስ ላይ የተጠመዱ የንግድና የመንግሥት የመገናኛ ብዙኃን ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጠን አሳሰበ፡፡ባለስልጣኑ እነዚህን ተቋማት ከመደገፍና ከማስተማር ባለፈ የይዘት ትንተና ውጤትን መሠረት በማድረግ እስከ መዝጋት የሚደርስእርምጃ እንደሚወስድም አስጠንቅቋል፡፡የመገናኝ ብዙኃን ሕዝባዊ አደራቸውን በልተው፣ እውነትን ረስተውና ሚዛናዊ ከሆነ የዘገባ ሥራ ይልቅ የመንግሥትን የፖለቲካ ፋላጎት ማራገብ ላይ ሲቆሙ፣ የዜጎችን መከባበርና አንድነት በመሸርሸር ጥላቻ ሲሰብኩ፣ ጉልበት ያለውን የሕዝብ ተቃውሞና ጥያቄ ጥላሸት ሲቀቡና ሲያጣጥሉ፣ የበቀል ቋንቋን ሲጠቀሙ ዜጎችን ለግጭት ይዳርጋሉ፡፡በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጠን የብሮድካስት አዋጅ ቁጥር 533/1999 ስር ለመተዳደር ቃል መሀላ በመውሰድ እየሠሩ ያሉ አንዳንድ የንግድና የመንግሥት የመገናኛ ብዙኃን በሕዝቦች መካከል የእርስ በርስ ግጭት ለማነሳሳት ሲሉ የይዘት ምንጭን ከአንድ ወገን ብቻ በማድረግና የዘገባ ሚዛናዊነትን በመናድ ሥራዎች ላይ እንደተጠመዱ ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ ባለስልጣኑ የተወሰኑ የግል እና የመንግሥት የመገናኛ ብዙኃንን በስም ጠቅሶ ትክክለኛ የመገናኛ ብዙኃንን ኃላፊነት እየተወጡ አለመሆኑን አስታውቋል፡፡", "passage_id": "a884cd4eb2a1b78be347530041a11236" }, { "passage": "በኢትዮጵያ ያሉ የግልም ሆኑ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን የመልካም አስተዳደር ዕጦትን ለመቅረፍ፣ ዋነኛ አጀንዳ አድርገው መሥራት እንዳለባቸው ተገለጸ፡፡የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ከሚዲያና ከኮሙዩኒኬሽን አመራሮች ጋር በመተባበር ‹‹ተፅዕኖ ፈጣሪ ሚዲያ ለመገንባት ያሉ ዕድሎች፣ ፈተናዎችና መፍትሔዎቻቸው›› በሚል መሪ ቃል ከመስከረም 21 ቀን እስክ 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ በጁፒተር ሆቴል ባዘጋጀው የሁለት ቀናት የውይይት መድረክ ላይ እንደተገለጸው፣ የመገናኛ ብዙኃን የመንግሥትን አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን የዕለት ተዕለት ሥራቸው አካል አድርገው መከታተል አለባቸው፡፡ በአገልግሎት አሰጣጡ ዙሪያ ጉድለቶች ከታዩ ወይም ተገልጋዩ ኅብረተሰብ በሚያደርሰው ጥቆማ ጉድለቶች እንዲታረሙ መጠየቅና ያለመታከት መከታተል እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡ከተፅዕኖ ፈጣሪ መገናኛ ብዙኃን አንፃር የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባሉባቸው ተጨባጭ እውነታዎች ዙሪያ ‹‹የኢትዮጵያ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪነት ከመልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ ግንባታ አንፃር›› የሚል ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አክሲዮን ማኅበር ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ብሩክ ከበደ፣ የመንግሥት አሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲኖረው፣ የኅብረተሰቡና የመገናኛ ብዙኃን ክትትል ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል፡፡መገናኛ ብዙኃን በምርመራ ዘገባ ላይ ትኩረት ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው የተናገሩት አቶ ብሩክ ሙስናን፣ ብልሹ አሠራርን፣ የተደራጁ ምዝበራዎችን ጊዜ ወስደው በመመርመር፣ በላቀ ሙያዊ ደረጃ ማጣራትና ማጋለጥ ትኩረቶች መሆን እንዳለባቸው አስረድተዋል፡፡ ሚዲያው ይህንን ሲያደርግ ራሱን በግንባር ቀደምትነት ከኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ተግባር ነፃ ማውጣት የመጀመሪያው ዕርምጃ መሆን እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ የሚዲያው አመራር ከተንጠራራ ፍላጎትና ከአድርባይነት ነፃ መሆን እንዳለበት፣ በተቋሙ ውስጥ ውስጣዊ ዴሞክራሲ እንዲኖር ማድረግ፣ ሁሉም አመራር የዘመናዊ ሚዲያ ዕውቀት ባለቤት እንዲሆን ማድረግ፣ ከየትኛውም አቅጣጫ የሚመጡ ውጫዊ ተፅዕኖዎችን ቀድሞ መገመትና ለመቋቋም ራስን ማዘጋጀት እንደሚገባ አክለዋል፡፡ በዋነኝነት የሚዲያ ተቋሙን ከኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና በንቃት መጠበቅና የውስጥ ንፅህናን በየጊዜው ማረጋገጥ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ጋዜጠኛው ከሁሉም በላይ ውግንናውን በዋነኝነት ለሕዝብ ማድረግ እንዳለበት የጠቆሙት አቶ ብሩክ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱንና ሕገ መንግሥቱን ማክበርና ማስከበር፣ በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ መሥራት፣ ሙያውን የስውር ፖለቲካ ተልዕኮ ማስፈጸሚያ ከማድረግ ተጠብቆ ሙያዊ ብቃቱን በሁሉም ዘርፍ ማሳደግ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡መንግሥት የመረጃ ነፃነትን በሁሉም ዘርፎች ማረጋገጥ፣ የሚዲያ ተቋማትን እንደ ሁነኛ የሕዝብ ድምፅ ማዳመጫ፣ መከታተያና መገንዘቢያ በመውሰድ መደበኛ መከታተያና ማስፈጸሚያ ሥርዓት መዘርጋት እንዳለበት በጥናታዊ ጽሑፋቸው የጠቆሙት አቶ ብሩክ፣ በሚዲያ ለሚቀርቡ የሕዝብ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች፣ ጥቆማዎችና የምርመራ ግኝቶች አፋጣኝ ምላሽ መስጠትና ማሳወቅ እንዳለበት አስረድተዋል፡፡የሚዲያ ነፃነት በማናቸውም የመንግሥት አካላትና ባለሥልጣናት የጎንዮሽ ወይም የጀርባ ጉንተላ፣ ማስፈራራትና ዛቻ ተፅዕኖ ሥር እንዳይወድቁ መንግሥት ጥብቅ ሥርዓት መዘርጋት እንዳለበት አቶ ብሩክ ተናግረዋል፡፡ ለሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች የክህሎትና የአመለካከት ዕድገት ሥልጠና ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንዳለበትም አክለዋል፡፡የመገናኛ ብዙኃን ከመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከጥገኛ ባለሀብቶች፣ ከጥገኛ ፖለቲከኞች፣ ከጥገኛ ማኅበራት፣ ከጥገኛ ምሁራን፣ ከደላሎችና ከሌሎችም ተግዳሮቶች እንደሚገጥሙት አቶ ብሩክ በጥናታቸው ዳሰዋል፡፡ የሕዝብ ግንኙነቶች አቅም ማነስ፣ የየተቋማቱ ቴክኖሎጂ የመጠቀም አናሳነትና የመንግሥት የማስፈጸም አቅም አናሳነትም የሚዲያው ተግዳሮቶች መሆናቸውን አክለዋል፡፡ፖሊስና ፍርድ ቤቶች ‹‹ለምን ተነካን?›› ብለው ሥልጠናቸውን ያላግባብ የመጠቀም ሁኔታ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በጥናቱ ጠቁመው፣ ‹‹አፈፍ›› እያደረጉ የማሰር ሥልጣናቸውን በጋዜጠኛ ላይ እንዳያደርጉ ወይም እንዳይተገብሩ የተለየ የሕግ ጥበቃ እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙኃን የሕዝብና የግል (ለዘብተኛና ጽንፈኛ) በሚል የተከፈሉ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ ብሩክ፣ በሁለቱም በኩል ጠንካራና ደካማ ጎኖች እንዳሉ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ሚናቸውን በብቃት እንዲወጡ እየገለጸና የመንግሥት የፀረ ኪራይ ሰብሳቢነትና መልካም አስተዳደር ማስፈን ፍላጎት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በጥናታቸው ያካተቱት አቶ ብሩክ፣ የሕዝቡ የዴሞክራሲ ባህል ዕድገትና ተሳትፎ መጎልበት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ሕዝቡ ባገኘው አጋጣሚ በነፃነት የመናገርና ሐሳቡን የመግለጽ ባህሉ እየዳበረ መሆኑን፣ የተማረው የኅብረተሰብ ክፍልና አዲሱ ትውልድ የነፃነትና የመብት ጥያቄው ከፍ እያለ መሆኑን፣ እንዲሁም ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃንን በማድመጥ ደረጃውን ከፍ እያደረገ ስለሆነ የመገናኛ ብዙኃን ክህሎትና ብቃት ሊታሰብበት እንደሚገባ አቶ ብሩክ አሳስበዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን ተናጋሪ ኅብረተሰብ መፍጠርና ኅብረተሰቡን የራሱ ባለጉዳይ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አክለዋል፡፡ ለኅብረተሰቡ ጥያቄዎች ትኩረት ሰጥቶ ማስተናገድና ምላሽ እንዲያገኝ ማድረግ፣ የመንግሥት ሐሳቦች፣ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና ዕቅዶች ላይ ኅብረተሰቡን በነፃነት በማሳተፍ አስተያየታቸውን በማካተት፣ ሙያው የመንግሥት አንደበት ከመሆን መላቀቅ እንዳለበትም በጥናቱ ተካቷል፡፡አቶ ብሩክ ካቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ ጋር ተመሳሳይነት ያለውና አጠቃላይ የመገናኛ ብዙኃን አሠራር ላይ ያተኮረ ‹‹የተፅዕኖ ፈጣሪ ሚዲያ ምንነትና በኢትዮጵያ ያሉት ዕድሎች፣ ፈተናዎችና መፍትሔዎቻቸው›› የሚል ጥናታዊ ጽሑፍ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙዩኒኬሽን ፋካልቲ መምህር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ለውይይት ቀርቧል፡፡ የውይይቱን መድረክ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘርዓይ አስገዶም በንግግር ከፍተዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ጌታቸው ረዳ የውይይቱ አስፈጻሚ ነበሩ፡፡", "passage_id": "7a49127523f77264703048dfa6cfcf93" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ህዳር 14፣ 2013 (ኤፍቢሲ) የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን የውጭ የመገናኛ ብዙኃን በተመለከተ እየወሰደ ያለውን ማስተካካያዎች በዝርዝር አስታወቀ፡፡ብሮድካስት ባለሥልጣኑ የውጭ የመገናኛ ብዙኃን በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል፡- የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ጥራቱ የተጠበቀ፣ በሃላፊነት ስሜት የሚንቀሳቀስ እና ነፃነቱ የተረጋገጠ አስተማማኝ የመገናኛ ብዙሃን የመገንባት እና የመቆጣጠር ዓላማን ይዞ የተቋቋመ አካል ነው፡፡የውጭ ሚዲያንም በተመለከተ የዘገባ ፈቃድና ዕውቅና ከመስጠት ባለፈ ከዘገባዎቻቸው በመነሳት የአዝማሚያ ትንተና (trend analysis) በመሥራት ዘገባዎቻቸው እውነትን መሠረት ያደረጉ እንዲሆኑ፤ ሚዛናዊና ተዓማኒነት ያላቸው ብሎም ሙያዊ ሥነ ምግባር የተላበሱ እንዲሆኑ  ለማድረግ የሚረዳ ግብረ መልስ ይሰጣል፤   የእርምት ዕርምጃ ይወስዳል፡፡ ይህ ሙከራም መሻሻሎችን ለማየት አስችሏል፡፡ይሁንና  የተሰጣቸውን ሙያዊ አስተያየት ችላ በማለት የተሳሳቱ ወይም ሚዛናዊነት የጎደላቸው ዘገባዎችን በመሥራት የቀጠሉ  አንዳንድ የውጭ የመገናኛ ብዙኃን አልጠፉም፡፡ ለምሳሌ ሮይተርስ፤ ቢቢሲ (አማርኛና እንግሊዝኛ ፕሮግራሞች)፤ የጀርመን ድምጽ የአማርኛ ፕሮግራም፤ እና አልጀዚራ (እንግሊዝኛ)  ተጠቃሽ ናቸው፡፡እነኚህ ሚዲያዎች በአገራችን ህጋዊ ፈቃድ የሌላቸው እንደ አዲስ ስታንዳርድ ያሉ ድረ-ገፆች እንዲሁም የጋዜጠኝነት ዕውቅናና ፈቃድ የሌላቸው እንደ ዊሊያም ዴቪሰን (William Davison) ያሉ ራሳቸውን የኢትዮጵያ ጉዳይ ተንታኝ አድርገው ያስቀመጡ ግለሰቦች  በቅርቡ የፌዴራል መንግስትና የሀገር መከላከያ ሰራዊት በህወኃት ጁንታ ላይ ህግን ለማስከበር እየወሰደ ያለውን ዕርምጃ አስመልክቶ ከሀቅ የራቁ መረጃዎችን የማሰራጨት፤ የኢትዮጵያ መንግስትን አስተያየት ያለማካተት እና ውጊያው የእርስበርስ ጦርነት እንደሆነ አስመስሎ የማቅረብ እንዲሁም እየተወሰደ ያለውን ዕርምጃ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የሰላም ኖቤል ሽልማት አሸናፊነት ጋር በማያያዝ ፌዴራል መንግስቱ ተገዶ የገባበት ሳይሆን ችግሩን በሰላምና በድርድር የመፍታት ፈቃደኝነት የጎደለው በማስመሰል እንዲሁም ሊፈጠር የሚችለውን ሰብዓዊ ቀውስ በተጋነነ መልኩ በመሳል ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያ ላይ  ጫና እንዲፈጠር የማድረግ አዝማሚያ አስተውለናል፡፡ስለሆነም የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን እየወሰደ ያለውን ማስተካካያዎች እንደሚከተለው ይገልፃል፡፡ሮይተርስ ፈቃዱ ተሰርዞ ከኢትዮጵያ እንደተባረረ በተለያዩ ሚዲያዎች የተገለፀው ስህተት ነው፡፡ እውነታው በኢትዮጵያ የሮይተርስ ቋሚ የዜና ወኪል የሆኑት ጋዜጠኛ ተቋማቸው የሠራውን ሚዛናዊነት የጎደለው ዘገባ አስመልክቶ ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በተደረገው ውይይት ወቅት ባሳዩት የመታረም ፈቃደኝነት ጉድለት እና ያልገባ ባህሪ ብሎም የሀገሪቱን ህግ አክብረው  ለመንቀሳቀስ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው  የድርጅታቸው የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ  ጋር በተደረገ ውይይት በ ምትክ ሮይተርስ ሌላ ቋሚ የዜና ወኪል እንዲመድብ ጥያቄ ቀርቧል፡፡  Nov.08/2020 “Ethiopia’s PM seeks to regain control over restive Tigray region” በሚል ርዕስ ሮይተርስ ባወጣዉ ዘገባ ግጭቱ ወደ እርስ በርስ ጦርነት ሊለወጥ እንደሚችል እና የብሄር መልክ የመያዝ ዕድል እንዳለዉ ጠቅሶ እንዲሁም የኢትዬጵያ መከላከያ ሰራዊት በየብሄር ተከፋፍሎ የመበተን ከፍተኛ አደጋ እንደተደቀነበትና ምልክቶችም እየታዩ እንደሆነ ይጠቅሳል፡፡ ሆኖም በጋዜጠኛ በኩል የመንግስትን አስተያየት ለማካተትም ይሁን ከገለልተኛ ወገን ለማጣራት ሙከራ አልተደረገም፡፡ William Davison የጋዜጠኝነት ዕውቅናና ፈቃድ የሌለዉ እንዲሁም በራሱ የኢትዮጵያ ጉዳይ ተንታኝነ ሆአድርጎ ያስቀመጠ ግለሰብ ነው፡፡ሆኖም ለበርካታ አመታት በኢትዬጵያ የBloomberg ሚዲያ ቋሚ የዜና ወኪል ሆኖ የሰራ ቢሆንም ከባለፉት ሶስት (3) ዓመታት ወዲህ ግን የዘገባ ፍቃዱን በራሱ ተነሳሽነት መልሶ የተሰናበተ መሆኑን እያረጋገጥን በተለያዩ የሚዲያ አዉታሮች በጋዜጠኝነት ስራዉ  ምክንያት ከሃገር እንደተባረረ ተደርጎ የሚሰራጨዉ መረጃ  ፍጹም ሃሰት መሆኑን ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡አልጀዚራን በተመለከተ በEnglish  ዘገባዎች ውስጥ በኢትዮጵያ መንግስት ወገን ያለን ምልከታ ሳያካትት በህውሓት ጁንታ ላይ የሚደረገውን የህግ ማስከበር ሂደት በአንድ ሃገር ብቻ የማያበቃ ነገር ግን መላ የአፍሪካ ቀንድን ሊያዳርስ የሚችል ጦርነት አድርጎ በመዘገብና በድርድር ጥያቄ ዙሪያ መንስግስት እምቢተኛ መሆኑን በማጉላት በሃገሪቱ ላይ የአለም አቀፍ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዲበረታ ሊያደርጉ የሚችሉ ሃላፊነት የጎላቸው ዘገባዎች ይታያሉ፡፡ ይህም በዋናነት Doha በሚገኘዉ የአልጀዚራ ዋና ማሰራጫ የእንግለዝኛ ስርጭት ክፍሉ የሚታይ ግድፈት መሆኑን በመረዳት በቀጣይ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስዱ ሪፖርት ተደርጎላቸዋል፡፡ለማሳያ ያህል፡-‹‹የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት እንዳሳሰባቸው ገለጹ። ውጥረቱን ለማርገብ እና ውዝግቡን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አፋጣኝ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባ ዋና ጸሐፊው አሳስበዋል።‹‹ በሚል ኖቬምበር 5/2020 ባሰራጨዉ ዘገባ በትክክል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ቃል መሆን ያለመሆኑን ማረጋገጥ በማያስችል መልኩ የቀረበ ከመሆኑም ባሻገር የህግ የበላይነትን ማስከበር ሳይሆን የእርስበርስ ግጭት እንደሆነ የሚያስመስል ዘገባ በመሆኑ ሊታረም የሚገባ መሆኑ ጀርመን ቦን ለሚገኙ ሃላፊዎች ተገልጾላቸዋል፡፡ቢቢሲም በአማርኛው ዘገባ ላይ  ሰኞ ኅዳር 07/2013 ዓ.ም  “ዛሬ ረፋዱ ላይ በትግራይ ክልል ርዕሰ ከተማ መቀሌ ውስጥ የአየር ጥቃት መፈጸሙን የከተማዋ ነዋሪዎችና የቢቢሲ ዘጋቢ ከስፍራው ገለጹ” በማለት ዘግቦ ሲያበቃ  በሁለተኛው ቀን ቀደም ሲል ያስተላለፈው ዘገባ የስህተት መረጃ መሆኑን ባግባቡ ሳይገልጽ በሌላ ዘገባ“የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማዕከል ዛሬ ማክሰኞ ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ ከመቀሌ ከተማ ውጪ ባሉ በተመረጡ ህወሓትን ኢላማ ያደረጉ መሆናቸውን ገልጿል” በማለት አሻሽሏል ። በሁለቱ ዘገባዎች መሃከል የሚታየው ልዩነት በትልቅ ሃላፊነትና ጥንቃቄ ሊሰራጭ የሚገባውና በሃገር ሰላም ዙሪያ ከፍተኛ እንድምታ ያለው ጉዳይ ላይ የሃሰት መረጃን በማን አለብኝነት ማስተላለፍ የውጪ ሚዲያዎች ልምድ እየሆነ መጥቷል፡፡ ይህም ሃገሪቱን በውጪው አለም ዘንድ ትክክል ያልሆነ የነበራዊ ሁኔታ ምስል እንዲኖር ስለሚያደርግ ሃገሪቱ በጥንቃቄ ልትይዘው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ቢቢሲ አማርኛ በአፋጣኝ ማስተካከያ እንዲያደርግ ሪፖርት ተደርጎለታል፡፡ እንደ ማጠቃለያም ከላይ የተጠቀሱት ዘጋቢዎች የሚያስራጯቸው መረጃዎች አለም አቀፍ የጋዜጠኝነት መርሆዎችን ያላገናዘቡ እና የግል አቋም የመያዝ አዝማሚያ የሚታይባቸው ናቸው፡፡  በሁሉም በመገናኛ ብዙሃኑ በተመሳሳይ ሁኔታ የሚታዩ ግድፈቶች፡- የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣንአዲስ አበባ", "passage_id": "49da3c2ee7c336600a4d0efa1519510a" } ]
27500d30d06a5bf8188201126cb3116d
8d1d8fe88244a3b22e9bf9c11c783efe
በአማራ ክልል በ1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር 14 የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ሊገነቡ ነው
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በመጭዎቹ ሦስት ዓመታት በአማራ ክልል ዝናብ አጠር እና ደረቃማ አካባቢዎች በ1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር 14 የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች እንደሚገነቡ ተገለጸ። ፕሮጀክቶቹ፣ በአማራ ክልል መካከለኛ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች ያለውን የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ለማሳደግ ያስችላል የተባለለት ይህ ፕሮጀክት በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ በሰሜን ወሎ፣ ማዕከላዊ ጎንደር፣ ደቡብ ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖች እንደሚገነባም ነው የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት የዘገበው። በዘገባው እንደተመላከተው፤ የፕሮጀክቱ አካል የሆኑት በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከተማ እና በሰሜን ወሎ ዞን ሰኞ ገበያ የሚገነቡት የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ የፊርማ ሥነ ሥርዓት የተከናወነ ሲሆን፤ የግንባታ ውሉ የፊርማ ሥነ ሥርዓትም በፕሮጀክቱ አስፈፃሚ የአማራ ክልል ውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ እና በሚገነባው የጢስ እሳት ኮንስትራክሽን ድርጅት መካከል ተካሂዷል። በወቅቱም፣ የአማራ ክልል ውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ማማሩ አያሌው እንደገለጹት፤ 14ቱ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች በአየር ንብረት አይበገሬነት የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ፕሮግራም የሚከናወኑ ሲሆኑ፤ ግንባታቸው በመጨዎቹ ሦስት ዓመታት ይጠናቀቃል ብለዋል። የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶቹን ገንብቶ ለማጠናቀቅ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ተመድቧል።በፕሮጀክቱ ግንባታ የፊርማ ሥነ ሥርዓት ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈጥሮ ሃብት ውኃ መስኖና ኢነርጂ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ፈትያ የሱፍ፣ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሽ በቀለ እና የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮ የተገኙ ሲሆን፤ ለፕሮጀክቶቹ ተፈፃሚነት የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የውኃ ልማት ኮሚሽን እና የአማራ ክልል ውኃ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ በጋራ እንደሚሰሩም ዶክተር ኢንጂነር ስለሽ በቀለ መናገራቸውን ነው አብመድ የዘገበው። አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37772
[ { "passage": "ባሕር ዳር፡ ግንቦት 19/2012 ዓ.ም (አብመድ) የአማራ ክልል የተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የዘጠኝ ወራት የመሠረተ ልማት ዘርፍ እቅድ አፈጻጸምን ዛሬ ገምግመዋል።ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዘርፉ 6 ሺህ 73 አነስተኛ የገጠር የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ለመገንባት ታቅዶ 716 ብቻ ተሠርተዋል፡፡ አፈጻጸሙም 11 በመቶ ብቻ ነው፡፡ አጠቃላይ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚነት አሁንም በብዙ ከተሞች ከፍተኛ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ቢሆንም ከነበረው በአንድ በመቶ ጭማሪ አሳይቶ 92 ነጥብ 19 መድረሱ በሪፖርቱ ቀርቧል።በመስኖ ልማት 1ሺህ 970 ሄክታር የሚያለሙ 11 ፕሮጀክቶች የጥናት ዲዛይን ሲሠራ ስድስት የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቁ ተገልጿል። በመንገድና ትራንስፖርት ዘርፍ በክልሉ በዘጠኝ ወራት 3 ሺህ 490 ኪሎ ሜትር ወቅታዊና መደበኛ ጥገና ለማካሄድ ታቅዶ 58 ነጥብ 7 በመቶ እንደተፈጸመ ተገምግሟል። በዘጠኝ ወራት የመንገድ ግንባታ አፈጻጸም የቅዱን ግማሽ ብቻ እንዳለው ተመላክቷል፡፡ በዕቅዱ የተያዙ አምስት ድልድዮች መገንባታቸው ደግሞ በስኬት ተጠቅሷል፡፡በክልሉ በህገ ወጥ መንገድ የተገነቡ ቤቶችን ሙሉ በሙሉ ለማፍረስ እቅድ ቢያዝም በዕቅዱ ከተያዙት 46 ሺህ 11 ህገወጥ ግንባታዎች ማፍረስ የተቻለው 3 ሺህ 436 ብቻ ነው። በ25 ከተሞች ሳይንሳዊና የተቀናጀ የከተሞች ጽዳትና አረንጓዴ ልማት ሥራዎችን ለመፈጸም የተያዘው እቅድም በስምንት ከተሞች 32 በመቶ ብቻ እንደተፈጠመ ተመላክቷል፡፡በሌላ በኩል በዓመቱ ለ 1ሺህ 700 የመኖሪያ ቤት ሥራ ማኅበራት 600 ሄክታር ቦታ ለመስጠት ታቅዶ አፈጻጸሙ 59 በመቶ እንደሆነ ተመላክቷል፡፡ በባሕር ዳር፣ ጎንደርና ደሴ ከተሞች ቦታ ባለመኖሩ ጥያቄው የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ መዝለቁም በሪፖርቱ ቀርቧል።", "passage_id": "fbf5a1c37a97232f7f4c2c0728094364" }, { "passage": "የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ከ8ሺ ሜጋ ዋት በላይ የሚያመነጩ ግድቦች ግንባታ ላይ መሆናቸዉን የዉሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር አስታወቀ ::ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ በሜጋ ፕሮጀክቶች ላይ እየተፈጠረ ያለዉ የእዉቀት፣ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሀገሪቱ በቀጣይ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሙሉ በሙሉ ለመስራት የምትችልበት መደላድል እየፈጠረ ነዉ ብለዋል::አገሪቱ አሁን ላይ  በማመንጨት ላይ ያለውን 4ሺህ 284 ሜጋ ዋት የኃይል አቅርቦት  እስከ ሁለተኛዉ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መጨረሻ ድረስ ወደ 17 ሺ ሜጋ ዋት ለማድረሰ እየተሰራ እንደሆነም ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል::የሀይል ፍላጎት አቅርቦቱን ለማሟላት እንደ ነፋስና ጸሐይ ኃይል ያሉ አማራጭ የታዳሽ ሀይል ምጮችን  የመጠቀሙ እንቅስቃሴም ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል ::ኢትዮጵያ ከውሀ ብቻ እስከ 45ሺ ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት ዓቅም እንዳላት ይታወቃል-(ኢቢሲ) ፡፡", "passage_id": "35f4a1d07b4fe3f882479109c156d4bc" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 19 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ጥቅም ላይ መዋል የሚችሉ 22 መካከለኛና ትላልቅ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶችን የአዋጭነት ጥናትና ዝርዝር ዲዛይን ስራዎች እንዲሁም ክለሳ በ2013 በጀት ዓመት በማከናወን ለግንባታ ምቹ የማድረግ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተገለፀ።የሁሉም ፕሮጀክቶች የአዋጭነት ጥናትና ዝርዝር ዲዛይን ማከናወኛ 255 ሚሊየን ብር በጀት መያዙ ተነግሯል።በበጀት ዓመቱ የሚጀመሩት 8 የመስኖ ልማት የአዋጭነት ጥናትና ዝርዝር ዲዛይን ፕሮጀክቶች በአማራ ክልል 2 ፣በደቡብ ክልል 2 ፣ በኦሮሚያ ክልል 3 እንዲሁም በሱማሌ ክልል 1 ናቸው።ፕሮጀክቶቹም የሽንፋ ፣የአንገረብ ፣የወይጦ፣የሽፌ፣የሞርሞራ ፣የታችኛው ገናሌ ፣የወይብ እና የቡልደሆ መሆናቸውን የመስኖ ልማት ኮሚሽን አስታውቋል።በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ 7 ፕሮጀክቶች የጥናትና ዲዛይን ስራቸው ተከልሶ ወደ ግንባታ እንዲገቡ ታቅዶ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።እነዚህ ፕሮጀክቶችም መገጭ ፣ግልገል አባይ ፣ጀማ ፣ብላቴ ፣ ዳቡስ ፣ ጎሎልቻ እና ገላና ግድብና መስኖ መሰረተ ልማት ሲሆኑ የጥናትና ዲዛይን ክለሳ ስራዎች እስከ ህዳር ወር ድረስ ለማጠናቀቅ ታቅዷል፡፡በ2012 በጀት ዓመት 7 የአዋጭነት ጥናትና ዝርዝር ዲዛይን የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶችን በ6 ክልሎች ማለትም በትግራይ፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ እና በደቡብ ክልሎች አንዳንድ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ሁለት የተከናወኑ ሲሆን በ2013 በጀት ዓመት ሁሉም ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል ፡፡#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "e32f23e1465337c7947e8c533682ee6b" }, { "passage": "የአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) የገቢ ማስገኛ ተቋማት ልማት ዳይሬክተር ዮሐንስ ታረቀኝ እንደገለጹት የክልሉን የልማት ሥራዎች ቀጣይነት ለማረጋገጥ በቀጣይ ዓመታት ቋሚ የገቢ ማስገኛ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል፡፡ማኅበሩ በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ከአባላቱ እና ከለጋሽ ድርጅቶች በሚሰበስበው ሀብት እያከናወነ እንደሚገኝ የገለጹት ዳይሬክተሩ የክልሉን ልማት ቀጣይነት ለማረጋገጥ ከአባላቱ እና ለጋሽ ድርጅቶች ገቢ በተጨማሪ ቋሚ የሀብት ማስገኛ ፕሮጀክቶን ለማቋቋም ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል፡፡ዳይሬክተሩ እንደገለጹት የመድኃኒት ፋብሪካ፣ የእንግዳ ማረፊያና ሁለገብ ሕንጻዎች፣ የሴቶች ንጽሕና መጠበቂያና የሕጻናት የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች በአዲስ ይገነባሉ፤ የዋንዛየ ፍል ውኃ እና የጢስ ዓባይ ‹ስፕሪንግ› ውኃ ፋብሪካዎች ደግሞ ማስፋፊያ ይደረግላቸዋል፡፡ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶን ሥራ የጀመረ ሲሆን አዳዲሶቹ ፕሮጀክቶች በዚህ ዓመት ጥናቶችን በማጠናቀቅ በሚቀጥለው ዓመት የግንባታ ሥራ እንደሚጀምር ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ 267 ሚሊዮን 935 ሺህ 248 ብር እንደሚጨርሱም ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡አልማ በቀጣይ ሦስት ዓመታት በሚያከናውነው ልማት 21 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለማሰባሰብ እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ ተገልጧል፡፡ ገንዘቡም በአብዛኛው በክልሉ የሚታየውን አጠቃላይ የትምህርት ቤቶች ደረጃ ለማሻሻል ሥራ ይውላል፡፡ ቀሪው የልማት ሀብት ደግሞ ለዘላቂ ልማት ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚውል ከማኅበሩ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ዘጋቢ፡- ዳግማዊ ተሰራ", "passage_id": "38a72c3fb85af2a50efd68e70a1a0db8" }, { "passage": " በተያዘው የ2007 በጀት ዓመት 514 የተለያዩ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እንደሚከናወኑ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።ባለስልጣኑ የ2006 በጀት ዓመት የስራ ክንውንና የ2007 ዕቅድን አስመልክቶ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት አድርጓል።የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዛይድ ወልደገብርኤል በዚህ ወቅት እንዳሉት በተያዘው በጀት ዓመት ለመንገድ ስራና ጥገና 29 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ተመድቧል።አቶ ዛይድ እንደገለጹት “ዕቅዱ አብዛኛውን የአገሪቱ ክፍል ማገናኘትን ዓላማ ያደረገና እስካሁን በፌደራል መንግስት የመንገድ ልማት ያልተዳሰሱ አካባቢዎችን ማዕከል አድርጎ የተዘጋጀ ነው”።ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የመጨረሻ ወቅት እንደመሆኑ ልዩ ትኩረትና ትርጉም እንደተሰጠውም አብራርተዋል።በዓመቱ 58 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ 13 ዋና መንገዶችን ማጠናከር፣ 135 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ 15 ዋና መንገዶችን ማሻሻልና 578 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ 57 የአገናኝ መንገዶችን የማሻሻል ስራዎች ይከናወናሉ።እንዲሁም 715 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን 81 የአገናኝ መንገዶች ግንባታና 118 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን 14 የመንገዶች ከባድ ጥገና ፕሮጀክቶችም የዚህ በጀት ዓመት የስራ አካል ናቸው።በበጀት ዓመቱ የመንገድ ልማት ዘርፍ ዕቅድ ከአዳዲስ ግንባታዎች በተጨማሪ፣ ከጎረቤት አገራት ጋር የሚያገናኙ መንገዶችን መገንባትና ማሻሻል፣ አገናኝ መንገዶችን መገንባት፣ ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ያለባቸውን መንገዶችም ማሻሻል እንደሚካተቱ አስረድተዋል።የግንባታ ኢንዱስትሪውን ጠንካራና ተወዳዳሪ ለማድረግና የመንገድ ግንባታው ጥራትና ተቀባይነት እንዲኖረው በትኩረት እንደሚሰራ በውይይቱ ተጠቅሷል።በፍጥነት እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሊደግፍ የሚችል የመንገድ አውታር በብዛት እና በጥራት ገንብቶ ለተጠቃሚው ለማቅረብ ብዙ መስራት እንደሚጠይቅም ነው የተገለጸው።በውይይቱ ላይ ከባለድርሻ አካላት ከተነሱና በአፈጻጸም ዙሪያ ከሚታዩ ችግሮች መካከል መንገዶች በጊዜ፣ በጥራትና በተያዘላቸው በጀት አለመጠናቀቃቸውን ይገኙበታል።በ2006 በጀት ዓመት አፈጻጸም ከግንባታ በፊትና በግንባታ ወቅት ለአካባቢ ጥበቃ ደህንነትና ለህብረተሰብ ነክ ጉዳዮች የሚሰጠው ትኩረት አናሳ እነደነበር በውይይቱ የተብራራ ሲሆን ይህንን ለመቅረፍ ግንባታ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይገባል ተብሏል።አዳዲስ መንገዶችን ከመገንባት ባሻገር የተገነቡ መንገዶችን ለመንከባከብ የሚሰጠው ትኩረት አናሳ በመሆኑም በተለይ አገር በቀል ተቋራጮች  በመንገድ ጥገና ላይ መሰማራት ይኖርባቸዋል ተብሏል።መንገዶች ጉዳት ደርሶባቸው አገልግሎት መስጠት ከማቋረጣቸው በፊትም ባለስልጣኑም ሆነ የሚመለከተው አካል አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ እንደሚገባውም ነው የውይይቱ ተሳታፊዎች ያሳሰቡት።የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በተጠናቀቀው የ2006 በጀት ዓመት ከ1 ሺህ 300 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታ አከናውኗል። (ኢዜአ)", "passage_id": "dbedf5dbe159ed87106ac2fc3e9da596" } ]
78197fea1447a37c06bef0376940b5c1
e3ed015bf8776e8da4df84d39dc225d2
ኢትዮጵያዊቷ አትሌት እገዳ ተጣለባት
ኢትዮጵያዊቷ የማራቶን ሯጭ እታፈራሁ ተመስገን አበረታች መድሃኒት ተጠቅማ በመገኘቷ ጊዜያዊ እገዳ ተጣለባት። አትሌት እታፈራሁ በዓለም አትሌቲክስ ገለልተኛ ሆኖ በተቋቋመው የአበረታች ንጥረ ነገሮች ምርመራ ቡድን በተደረገላት ምርመራ ብቃቷን ከፍ የሚያደርግ መድሃኒት ተጠቅማ በመገኘቷ እገዳው እንደተጣለባት ኢንሳይድ ዘጌምስ ዘግቧል። የሰላሳ ዓመቷ አትሌት እታፈራሁ ባለፈው ሰኔ በኦታዋ ማራቶን ተሳትፋ 2፡28፡44 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ የሚታወስ ሲሆን ከወር በፊት በቶሮንቶ ማራቶን 2፡27፡ 21 በሆነ ሰዓት ስምንተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወቃል። እ ኤ አ በ2018 በሜክሲኮ ማራቶን አትሌቷ 2፡40፡10 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችላለች። አትሌት እታፈራሁ የተደረገላትን ምርመራ ማለፍ ባለመቻሏ በየትኛውም ስፖርት ላልተወሰነ ጊዜ ተሳታፊ እንዳትሆን ጊዜያዊ እገዳ የተጣለባት ሲሆን የዓለም አትሌቲክስና ገለልተኛው የምርመራ ቡድን ከአበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነት ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ህግጋቶችን መሰረት አድርገው ወደ ፊት በቋሚነት ቅጣት እንደሚያስተላልፉ ዘገባው አመልክቷል። ከወር በፊት በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የአስር ሺ ሜትር አሸናፊ የሆነው ኢትዮጵያዊው አትሌት ብርሃኑ ፀጉ የተደረገለትን የአበረታች መድሃኒት ምርመራ ማለፍ ባለመቻሉ ተመሳሳይ እገዳ እንደተጣለበት ይታወሳል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአትሌቲክሱ አበረታች መድሃኒት ወይም ንጥረ ነገሮች ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ ሩሲያን የመሳሰሉ ታላላቅ አገራት ከታላላቅ ውድድሮች እስከመ ታገድ ደርሰዋል። እነዚህ አገራት አትሌ ቶቻቸው በብዛት አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆነው ከመገኘታቸው ጋር ተያይዞ በመንግሥት ጭምር ይደገፋሉ በሚል ከውድድሮች መታገ ዳቸው ይታወቃል። የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ኤጀንሲ እነ ሩሲያን በቀጣበት ወቅት ኢትዮጵያና ኬንያ አደጋው በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሰጋቸው በማሳወቅ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ምክረ ሃሳብ ሰጥቷቸው ነበር። ሁለቱ አገራት በተለይም ኢትዮጵያ ለጉ ዳዩ ትኩረት ሰጥታ በመስራት አበረታች ውጤት ማስመዝገቧም በኤጀንሲው ጭምር ተመስክሮላታል። ያም ሆኖ ስጋቱ ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ለማለት አይቻልም። ባለፈው ዓመት የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያና ኬንያን በአበረታች መድሃኒት (ዶፒንግ) ምክንያት ስጋት ካለባቸው አገራት ቀዳሚውን ደረጃ እንደሚይዙ ማሳወቁ ይታወሳል። ዘንድሮም ሁለቱ አገራት በአበረታች መድሃኒት ስጋት ቁንጮውን ደረጃ መያዛቸው እንደማይቀር እየወጡ ያሉ መረጃዎች ጠቋሚ ናቸው። ለዚህም ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ አምስት የአፍሪካ አገራት አትሌቶች አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆነው መገኘታቸው ማሳያ ተደርጓል። ቤላሩስና ዩክሬን ሁለቱን የአፍሪካ አገራት ተከትሎ ስማቸው ከቁንጮዎቹ ተርታ ተፅፏል። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለይም በግል ውድድሮች ብቻ የሚታወቁት አልፎ አልፎ በአበረታች መድሃኒት ሲቀጡ ይታያል። ይሁን እንጂ አገርን ወክለው በሚወዳደሩ አትሌቶች ይህ ቅሌት አይታይም ማለት ይቻላል። ባለፈው ክረምት በሞሮኮ ራባት በተካሄደው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን ወክሎ በአስር ሺ ሜትር ወርቅ ማጥለቅ የቻለው ብርሃኑ ፀጉ ኢፒኦ የተባለ ንጥረ ነገር ተገኝቶበት ላልተወሰነ ጊዜ ከስፖርቱ ታግዷል። ይህ የሃያ ዓመት አትሌት ባለፈው ወር በኮፐንሃገን ግማሽ ማራቶን ላይ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል። ብርሃኑ ሔንግሎ በተካሄደው የዓለም ቻምፒዮና የኢትዮጵያውያን ማጣሪያ ውድድር ላይ 10ሺ ሜትሩን 27፡00፡73 በሆነ ሰዓት ማጠናቀቅ ችሏል። ብርሃኑ በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ሲያሸንፍ ኤርትራዊው አሮን ክፍሌና ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ጀማል ይመር ተከትለውት መግባታቸው ይታወሳል። ብርሃኑ የወርቅ ሜዳሊያውን ተነጥቆ ለኤርትራዊው አትሌት፣ የብር ሜዳሊያው ደግሞ ለጀማል ይመር የሚሰጥ ሲሆን አራተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ኬንያዊው ኤድዊን ሦይ የነሐስ ሜዳሊያ ሊያገኝ እንደሚችል መረጃዎች እየወጡ ነው። በአዲስ አበባ አበረታች መድሃኒቶች በስታድየም አካባቢ ካለ ሐኪም ማዘዣ ጭምር እንደሚሸጡ የእንግሊዝ ሚዲያዎች መዘገባቸውን ተከትሎ የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያን ማስጠንቀቁ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ፅሕፈት ቤትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቶች የተለያዩ ትምህርቶችን እየሰጡ ይገኛሉ።አዲስ ዘመን ኅዳር 18/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23270
[ { "passage": "ጎረቤታሞቹ የምስራቅ አፍሪካ የረጅም ርቀት ፈርጦች ኬንያና ኢትዮጵያ በአትሌቲክሱ ያላቸውን መልካም ስም ያህል በስፖርቱ ትልቅ አደጋ እያንዣበበባቸው ይገኛል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአትሌቲክሱ አበረታች መድሃኒት ወይም ንጥረ ነገሮች ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ ሩሲያንን የመሳሰሉ ታላላቅ አገራት ከታላላቅ ውድድሮች እስከመታገድ ደርሰዋል። እነዚህ አገራት አትሌቶቻቸው በብዛት አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆነው ከመገኘታቸው ጋር ተያይዞ በመንግስት ጭምር ይደገፋሉ በሚል ከውድድሮች መታገዳቸው ይታወቃል። የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ኤጀንሲ እነ ሩሲያን በቀጣበት ወቅት ኢትዮጵያና ኬንያ አደጋው በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሰጋቸው በማሳወቅ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ምክረሃሳብ ሰጥቷቸው ነበር። ሁለቱ አገራት በተለይም ኢትዮጵያ ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥታ በመስራት አበረታች ውጤት ማስመዝገቧም በኤጀንሲው ጭምር ተመስክሮላታል። ያም ሆኖ ስጋቱ ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ለማለት አይቻልም። ባለፈው ዓመት የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያና ኬንያን በአበረታች መድሃኒት(ዶፒንግ) ምክንያት ስጋት ካለባቸው አገራት ቀዳሚውን ደረጃ እንደሚይዙ ማሳወቁ ይታወሳል። ዘንድሮም ሁለቱ አገራት በአበረታች መድሃኒት ስጋት ቁንጮውን ደረጃ መያዛቸው እንደማይቀር እየወጡ ያሉ መረጃዎች ጠቋሚ ናቸው። ለዚህም ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ አምስት የአፍሪካ አገራት አትሌቶች አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆነው መገኘታቸው ማሳያ ተደርጓል። ቤላሩስና ዩክሬን ሁለቱን የአፍሪካ አገራት ተከትሎ ስማቸው ከቁንጮዎቹ ተርታ ተፅፏል። የአስራ ስምንት ዓመቷ ኬንያዊት አትሌት አንጌላ ሙንጉቲ ከቀናት በፊት አበረታች መድሃኒት ተጠቅማ በመገኘቷ እገዳ ተጥሎባታል። በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የስምንት መቶ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊ የሆነችው ይህች አትሌት በዚህ ወንጀል የተያዘች አርባ አራተኛዋ ኬንያዊት አትሌት ሆናለች። አትሌቷ ባለፈው ዓመት አርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደው የወጣቶች ኦሊምፒክም በስምንት መቶ ሜትር አገሯን ወክላ መወዳደር ችላለች። የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች መድሃኒት አዋጅ የትኛውም አትሌት በውስጡ ለተገኘ አበረቻች ንጥረ ነገር ሃላፊነቱን ይወሳዳል። ይህችም አትሌት ኖራንድሮስቴሮን የተባለ አበረታች ንጥረነገር ተጠቅማ መገኘቷ ተረጋግጣል። ሙንጉቲ በስምንት መቶ ሜትር 2፡06፡21 የሆነ የራሷ ፈጣን ሰዓት ያላት ሲሆን ባለፈው ዓመት በኬንያ ከሃያ ዓመት ቻምፒዮና ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቅ ችላለች። ፊሊፕ ሳንጋ ኪሙታይ የተባለው የሰላሳ ስድስት ዓመት ኬንያዊ አትሌት ቴስቴስትሮን የተባለ አበረታች ንጥረነገር ተጠቅሞ የተገኘ አርባ ሦስተኛው ኬንያዊ አትሌት ነው። የዚህ አትሌት ምርመራ በሂደት ላይ ሲሆን ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ከስፖርቱ ለአራት ዓመታት ሊታገድ እንደሚችል ታውቋል። ኪሙታይ በማራቶን 2፡06፡07 ሰዓት ያለው ሲሆን እኤአ 2011 ላይ በፍራንክፈርት ማራቶን ያስመዘገበው ይህ ሰዓት በውድድር ዓመቱ አስራ ሦስተኛው ፈጣን አትሌት አድርጎት ነበር። ይህ አትሌት ባለፈው ዓመት በጎልድ ኮስት ማራቶን አምስተኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ 2፡11፡44 ሰዓት ማስመዝገብ ችሏል። በሆንግኮንግ ማራቶንም አስረኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡15፡31 ሰዓት ተመዝግቦለታል። በዚህ ወር በአበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነት ቅጣት የተላለፈበት ወይንም የተገኘበት አርባ ሁለተኛው ኬንያዊ አትሌት ቪንሰንት ኪፕሴጊች ነው። ይህ የሰላሳ ዓመት አትሌት ቀደም ሲል የተጠቀሰው ኬንያዊ አትሌት ኪሙታይ በጎልድ ኮስት ማራቶን አምስተኛ ሲያጠናቅቅ አራተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ ችሏል። 2፡09፡59 የሆነ የራሱ ፈጣን ሰዓትም አለው። ሚያዝያ ወር ላይም በቬና ማራቶን ሰባተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡10፡02 አስመዝግቧል። በተመሳሳይ ከዓመት በፊት በሆኖሉሉ ማራቶን ሦስተኛ ሆኖ ጨርሷል። ኢትዮጵውያን አትሌቶች በተለይም በግል ውድድሮች ብቻ የሚታወቁት አልፎ አልፎ በአበረታች መድሃኒት ሲቀጡ ይታያል። ይሁን እንጂ አገርን ወክለው በሚወዳደሩ አትሌቶች ይህ ቅሌት አይታይም ማለት ይቻላል። ባለፈው ክረምት በሞሮኮ ራባት በተካሄደው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን ወክሎ በአስር ሺ ሜትር ወርቅ ማጥለቅ የቻለው ብርሃኑ ፀጉ ኢፒኦ የተባለ ንጥረ ነገር ተገኝቶበት ላልተወሰነ ጊዜ ከስፖርቱ ታግዷል። ይህ የሃያ ዓመት አትሌት ባለፈው ወር በኮፐንሃገን ግማሽ ማራቶን ላይ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል። ብርሃኑ ሔንግሎ በተካሄደው የዓለም ቻምፒዮና የኢትዮጵያውያን ማጣሪያ ውድድር ላይ 10ሺ ሜትሩን 27፡00፡73 በሆነ ሰዓት ማጠናቀቅ ችሏል። ብርሃኑ በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ሲያሸንፍ ኤርትራዊው አሮን ክፍሌና ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ጀማል ይመር ተከትለውት መግባታቸው ይታወሳል። ብርሃኑ የወርቅ ሜዳሊያውን ተነጥቆ ለኤርትራዊው አትሌት፣ የብር ሜዳሊያው ደግሞ ለጀማል ይመር የሚሰጥ ሲሆን አራተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ኬንያዊው ኤድዊን ሦይ የነሐስ ሜዳሊያ ሊያገኝ እንደሚችል መረጃዎች እየወጡ ነው። በአዲስ አበባ አበረታች መድሃኒቶች በስቴድየም አካባቢ ካለ ሃኪም ማዘዣ ጭምር እንደሚሸጡ የእንግሊዝ ሚዲያዎች መዘገባቸውን ተከትሎ የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያን ማስጠንቀቁ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ፅሕፈት ቤትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቶች የተለያዩ ትምህርቶችን እየሰጡ ይገኛሉ። በቅርብ ወራት አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆኖ በመገኘት ስማቸው ከተዘረዘሩ አፍሪካውያን መካከል ሞሮኳዊው ሙስጠፋ ኤል አዚዝ አንዱ ነው። ይህ አትሌት ለአራት ዓመታት ከስፖርቱ እንዲርቅ ቅጣት የተጣለበት ሲሆን 2014 የአፍሪካ ቻምፒዮና ላይ በአስር ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ በማጥለቁ ይታወቃል። ይህ የሰላሳ ሦስት ዓመት አትሌት ባለፈው ሰኔ ክሮሽያ ውስጥ በተካሄደ የጎዳና ላይ ውድድር አበረታች ንጥረነገር ተጠቅሞ በመገኘቱ እገዳው እንደተላለፈበት ተነግሯል። ሞሮኮ በአበረታች መድሃኒት አደጋ ውስጥ ከሚገኙ አገራት መካከል ትጠቀሳለች። ይሁን እንጂ በዚህ አደጋ እጅግ ችግር ውስጥ ካሉ አገራት ተርታ በ2017 የወጣች ቢሆንም አሁን ተመልሳ ገብታበታለች።አዲስ ዘመን ጥቅምት 17/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "7c84ac503336f93af8e8b10eea9d4592" }, { "passage": "\nበኬንያ፥ ሕገወጥ የጉልበት ሰጪ መድሃኒት መጠቀም ቅሌት መከሰት፥ ሀገሪቱ በአትሌቲክስ በአለም ገናና የሆነችበትን ታሪኳን እንዳያበላሽ ተሰግቷል። በተለይ አሁን በመጨረሻ በሁለት የቦስተን እና የቺካጎ ማራቶኖች ቀደም ሲል ደግሞ በስቶክሆልም፥ ፓሪስ፥ ሚላን እና ሊዝበን ያሸነፈችው Rita Jeptoo በተደረገላት ምርመራ ደሟ ውስጥ የተከለከለ ጉልበት ሰጪ መድሃኒት መኖሩ ከተረጋገጠ በሗላ ሁኔታው በእጅጉ አሳሳቢ ሆኗል።በጠቅላላው 36 የኬንያ አትሌቶች ባለፉት ሁለት አመታት የተደረገላቸውን የደም ምርመራ ሳያልፉ ቀርተዋል።", "passage_id": "441bf7b55a0715c5a5c6aac459fa40c7" }, { "passage": "ሻለቃ ደራርቱ ቱሉ፣ ሰለሞን ባረጋና ዱቤ ጂሎ\n\nበካታር ዶሃ እየተካሄደ ባለው 17ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ በማራቶን ውድድር ላይ የተሳተፉት አትሌቶች ለቀጣዮቹ ሦስት ወራት እረፍት አድርገው እንዲያገግሙ እንጂ እገዳ አለመሆኑን ገልጸዋል። \n\n• ቀነኒሳ 'ከሞት እንደመነሳት' ነው ባለው ሁኔታ ማራቶንን አሸነፈ\n\n• በዶሃ የሴቶች ማራቶን ሦስት ኢትዮጵያውያን ሯጮች አቋርጠው ወጡ \n\nውሳኔው ከ42 ኪሎሜትሮች በላይ በሚሮጥበት ከባድ በሚባለው የማራቶን ውድድር ላይ የሚሳተፉ ሯጮችን ጤንነትና ደህንነት ለመጠበቅ የሚወሰድ ተቀባይነት ያለው እረፍት ነው ብለዋል ዱቤ ጅሎ። \n\nአትሌቶች የሦስት ወራት የማገገሚያ ጊዜ እንዲያገኙ ማድረግ በዓለም አቀፍ የውድድር ሕግና ደንብ ውስጥ ተቀባይነት ያለውና በሌሎችም ሃገራት የሚሰራበት እንደሆነ አመልክተዋል። \n\nለሦስት ወራት ከውድድር እርቆ የሚወሰደው እረፍት ሁሉንም በማራቶን ውድድር የተሳተፉ አትሌቶችን የሚመለከት መሆኑን የጠቀሱት የቴክኒክ ዳይሬክተሩ፤ በተለይ በዶሃ ያለው ከባድ ሙቀት ላይ ለተወዳደሩ አትሌቶች እረፍቱ በጣም አስፈላጊያቸው ነው ብለዋል ለቢቢሲ። \n\nባለፈው አርብ ሌሊት በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ላይ ተሳታፊ የነበሩት ኢትዮጵያዊያን ሯጮች በነበረው ከፍተኛ ሙቀት ምክንያት ውድድሩን አቋርጠው መውጣታቸው የሚታወስ ሲሆን እነርሱ ብቻ ሳይሆኑ በርካቶችም ለማቋረጥ ተገደው ነበር።\n\n• ''በኳታር የኢትዮጵያ ቡድን በሙቀቱ ተቸግሯል'' የቡድኑ መሪ \n\n• የሞ ፋራህ የቀድሞ አሠልጣኝ ከአትሌቲክስ ታገዱ\n\nስለዚህም የማራቶን ሯጮቹ ከነበሩበት ከባድ ሁኔታ እንዲያገግሙ በፌዴሬሽኑ ደንብ መሰረት ለሦስት ወራት ልምምድ እየሰሩ እረፍት እንዲያደርጉና ከውድድር እንዲርቁ መደረጉን አመልክተዋል። \n\nበሴቶቹ የማራቶን ውድድር ላይ ተሳታፊ የነበሩትና አቋርጠው ለመውጣት የተገደዱት ሯጮች የጤንነት ሁኔታን በተመለከተ በስፍራው የሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ ዱቤ ጅሎን ጠይቆ ባገኘው መረጃ መሰረት አንዷ ከገጠማት ቀላል ችግር በስተቀር ሁሉም በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ታውቋዋል። \n\nበዶሃ ባለው ከባድ ሙቀት ምክንያት በእኩለ ሌሊት ጎዳና ላይ በሚደረጉት የማራቶንና የእርምጃ ውድድሮች ተሳታፊዎች ላይ ከባድ ጫናን የሚያሳድር እንደሆነ የተናገሩት የቴክኒክ ዳይሬክተሩ ስታዲየም ውስጥ የሚደረገው ግን ብዙም አስቸጋሪ እንዳልሆነ ገልጸዋል። \n\n ", "passage_id": "d2204bfcaab75ac5445a6e7c091cdb46" }, { "passage": "ለአለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ለመናገር ፈቃደኛ ካልሆነች ትታገዳለች የሚል ውዝግብን ተከትሎ ነው በፈረንሳይ ኦፕን እንደማትወዳደር ያሳወቀችው።\n\nይህንን ባሳወቀችበት የትዊተር መልዕክትም ናኦሚ በጭንቀት (ዲፕረሽን) ህመም እየተሰቃየች እንደሆነ አስፍራለች።\n\nህመሟም የጀመረው ከሶስት አመት በፊት በሜዳ ቴኒስ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠውን የመጀመሪያዋን ግራንድ ስላም ካሸነፈች ጀምሮ ነው።\n\nየ23 አመቷ አትሌት የአዕምሮ ጤንነቷን ለመጠበቅ በሮላንድ ጋሮስ ጋዜጣዊ መግለጫ አልሳተፍም ያለችው ባለፈው ሳምንት ነበር።\n\nባለፈው ሳምንት እሁድ ከሮማኒያዊቷ ፖትሪሺያ ማሪያ ቲግ ጋር በነበረው ውድድር በአሸናፊነት ያጠናቀቀችበት ጨዋታ ተከትሎ ከሚዲያዎች ጋር ቆይታ አላደርግም በማለቷ 15 ሺህ ዶላር ተቀጥታለች።\n\nበዚያኑ ቀን የግራንድ ስላም ውድድር አዘጋጆች ባወጡት የጋራ መግለጫ አትሌቷ ሚዲያ አላናግርም በሚል ባህርይዋ ከቀጠለች ከጨዋታዎች እንደምትታገድ አስጠንቅቀው ነበር።\n\nአትሌቷም በትናንትናው ዕለት ከፈረንሳይ ኦፕን ራሷን እንዳገለለች ገልፃ \"ለተወሰነ ጊዜም ከሜዳ ራሴን አርቄያለሁ \" ብላለች።\n\n\"ትክክለኛው ወቅት ሲመጣ ከውድድር አዘጋጆች ጋር ለአትሌቶች፣ ለሚዲያዎችና ለተመልካቾች በምን መንገድ ውድድሮችን ማሻሻል እንችላለን የሚለው ላይ መወያየት እፈልጋለሁ' ብላለች።\n\nየፈረንሳይ ቴኒስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ጊለስ ሞሬቴን የናኦሚን ራሷን ከውድድር ማግለል አስመልክቶ \"አሳዛኝ\" ብለውታል።\n\n\"ናኦሚ በገጠማት ሁኔታ ሃዘን ተሰምቶናል። በፍጥነትም እንድታገግም ምኞታችንን እየገለፅን በሚቀጥለው አመት ውድድራችን እናያታለን ብለን እንጠብቃለን\" ብለዋል ።\n\n\"ሁሉም የግራንድ ስላምስ ውድድሮች ማለት ደብልዩ ቲ ኤ፣ ኤቲፒና አይቲኤ ለአትሌቶች ጤና ቅድሚያ በመስጠት በሌሎችም ዘርፎች አትሌቶች የሚሻሻሉበትን መንገድ እንቀይሳለን። ከዚህም ጋር ተያይዞ አትሌቶች ከሚዲያዎች ጋር ያላቸው ግንኙነቶች እንዲሻሻሉ ስንሰራ ነበር። አሁንም እንሰራለን\" በማለት አስረድተዋል።\n\n ", "passage_id": "98e79e89608a31b2e4345b3b1519b4f7" }, { "passage": " ግዙፉ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ በአሜሪካ ፖርትላንድ ኦሪገን ያለውን የአትሌቲክስ ፕሮጀክት መዝጋቱን አስታወቀ። የፕሮጀክቱ አሰልጣኝ የሆነው አልቤርቶ ሳላዛር ከአበረታች መድኃኒት ዓለምአቀፍ ሕግጋቶች መጣስ ጋር ተያይዞ ከሳምንት በፊት ከማንኛውም ስፖርት ለአራት ዓመታት መታገዱ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ ናይኪ ፕሮጀክቱን ለመዝጋት እንደወሰነ ረነርስ ወርልድ ከትናንት በስቲያ ምሽት ዘግቧል። አሰልጣኝ አልቤርቶ ሳላዛር በፕሮጀክቱ የሚያሰለጥናቸውን አትሌቶች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ አበረታች መድኃኒት እንዲጠቀሙ ያደርጋቸዋል በሚል ከስፖርቱ መታገዱን ተከትሎ በፕሮጀክቱ የታቀፉ አትሌቶች ጥያቄ ውስጥ መግባታቸው አልቀረም። የናይኪ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ፓርከር ለረነርስ ወርልድ እንደገለፁት፣ የፕሮጀክቱ አትሌቶች ባልተረጋገጠ አሉባልታ ከአበረታች መድኃኒትተጠቃሚነት ጋር ስማቸው መነሳቱ ያላቸውን እምቅ አቅም ተጠቅመው በልምምድና ውድድሮች ላይ ትኩረት እንዳያደርጉ ተፅዕኖ ስለሚፈጥርባቸው ፕሮጀክቱን መዝጋት አስፈላጊ ሆኗል። ስለዚህም ናይኪ ኩባንያ የፕሮጀክቱን አትሌቶች በሚፈልጉትና ትክክል ነው ብለው በሚያምኑት አሰልጣኝና የሥልጠና ሂደት እንዲከታተሉ በማድረግ ድጋፉን ከውጪ ሆኖ እንደሚቀጥልበት ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። የፕሮጀክቱን በርካታ አትሌቶች የሚያሰለጥኑት ፒት ጁሊያን ከአበረታች መድኃኒት ጋር በተያያዘ ስማቸው የማይነሳ ከመሆኑም ባሻገር የዓለም አትሌቲክስ ጋር ጥሩ ግንኙነት እንዳላቸው ይነገራል። የናይኪ ኦሪገን ፕሮጀክት ሲዘጋ የእኚህ አሰልጣኝ ዕጣፈንታ ምን እንደሚሆን የተገለፀ ነገር የለም። በቅርቡ በተጠናቀቀው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በአስር ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ማሸነፍ የቻለው ኢትዮጵያዊው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻን ጨምሮ የአስርና አንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ቻምፒዮኗ ትውልደ ኢትዮጵያዊት የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን የናይኪ ኦሪገን አትሌቲክስ ፕሮጀክት ሰልጣኞች ናቸው። ነገ በሚካሄደው የቺካጎ ማራቶን የሚወዳደሩት አሜሪካውያኑ ጋለን ሩፕና ጆርዳን ሃሴይም የዚሁ ፕሮጀክት ፍሬዎች ናቸው። የሦስት የዓለም ቻምፒዮናዎችና የሁለት ኦሊምፒኮች የአስርና አምስት ሺ ሜትር ቻምፒዮኑ እንግሊዛዊው አትሌት ሞ ፋራህን በነገው የቺካጎ ማራቶን ለአሸናፊነት የሚጠበቅ የቀድሞ የናይኪ ኦሪገን አትሌቲክስ ፕሮጀክት ውጤት መሆኑ ይታወቃል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆነው የአትሌቲክስ ስፖርት አሠልጣኝ አልቤርቶ ሳላዛር የተከለከሉ አበረታች ቅመሞችን ከቦታ ቦታ ማዘዋወርን\n(Trafficking) ጨምሮ የፀረ-ዶፒንግ እንቅስቃሴውን በማወክ\n(Tampering) እና በተለያዩ የፀረ-ዶፒንግ የሕግ ጥሰቶች ተጠርጥሮ ጉዳዩ በአሜሪካ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ (USA­DA) ሲጣራ ቆይቷል። በዚህም መሠረት ግለሰቡ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ለአራት ዓመታት በስፖርቱ ውስጥ እንዳይሳተፍ እገዳ ተጥሎበታል። ኢትዮጵያውያን አትሌቶችና የስፖርት ባለሞያዎችም ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ ከአሰልጣኝ አልቤርቶ ሳላዛር ጋር የሚኖራቸውን ቀጥተኛም ይሁን ቀጥተኛ ያልሆነ ግንኙነት ማቋረጥ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽሕፈት ቤት ማሳሰቡ ይታወሳል።አዲስ ዘመን ጥቅምት 1/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "ba423af6511abb3fd29996df2ac6a138" } ]
3e0e3de62e427a0415be59f5259e0d2e
14de21769223b2b3081f492260b42bb7
”ለመከላከያ ምንም ድጋፍ ቢደረግ ለሀገርና ለህዝብ የዋለውን ውለታ መመለስ አይቻልም” – አቶ የሺዋስ አሰፋ የኢዜማ ሊቀመንበር
ሶሎሞን በየነአዲስ አበባ:- ለአገር መከላከያ ሠራዊቱ የሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ ሞራል ለመስጠትና አጋርነትን ለማሳየት ያህል ካልሆነ በስተቀር ሠራዊቱ አጥንቱን ከስክሶ አገር እንዳዳነው፣ ደሙን አፍሶ የኢትዮጵያን ሃጢያት እንዳጠበው እንደማይሆን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ ገለጹ።አቶ የሺዋስ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ እንደገለጹት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሰሜን ዕዝ ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ የአገር መከላከያ ሠራዊት ህግን ለማስከበርና የአገርን ህልውና ለማዳን መስዋዕትነት ከፍሏል፤ እየከፈለም ይገኛል። ይሄን ተከትሎም ኅብረተሰቡ ለመከላከያ ሠራዊቱ ሰፊ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ሆኖም በዚህ መልኩ የሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ ለሠራዊቱ ሞራል ለመስጠትና አጋርነትን ለማሳየት ያህል ካልሆነ በስተቀር ማንም ምንም አይነት ድጋፍ ቢያደርግ መከላከያ ሠራዊቱ አጥንቱን ከስክሶ አገር እንዳዳነው፣ ደሙን አፍሶ የኢትዮጵያን ሃጢያት እንዳጠበው አይሆንም።በአገር መከላከያ ላይ የተፈጸመው ክህደት እኛ ካልመራን አገር ትጠፋለች ከሚል አስተሳሰብ የመነጨ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ የሺዋስ፤ ይህ አጥፊ ቡድን እራሱ የቆሰቆሰውን የኤርትራ ጦርነት ምክንያት አድርጎ የአገሪቱ ትልቁ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዲፖ፣ ብረት ለበስ ወታደራዊ ኃይል፣ የአገሪቷ መካናይዝድ ጦር፣ ስምንት ትልልቅ ክፍለጦር ያሁሉ የጦር መሳሪያ በአንድ ቦታ በማከማቸት የየራሱን ጉልበት ሲያጠናክር መቆይቱን ተናግረዋል። የጁንታው ቡድን በህዝብ ቁጣ አንድ ቀን ስልጣኔን አጣለሁ ብሎ ስለሚሰጋ ሰልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ ለጦርነት ሲዘጋጅ እንደቆየና ጉድጓድ ሲቆፍር፣ ነዳጅና የጦር መሳሪያ ሲያከማች ጊዜውን እንዳጠፋ በመግለጽም፤ ከዚህ ባሻገር በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ከለውጥ መንግሥቱ ጋር ተባብሮ ከመስራት ይልቅ በሰበብ አስባቡ ጠብ እየፈለገ ሁከት ለመፍጠር ሲሞክር መቆየቱን አብራርተዋል። በመጨረሻም ቡድኑ ለ21 ዓመታት ያህል ድንበር ሲጠብቅ የቆየውን ሠራዊት ከትግራይ አይወጣም በማለት በሠራዊቱና በመንግሥት ላይ ጫና ለማሳረፍ ከመሞከሩም ባሻገር፤ ለትግራይ ህዝብ አለኝታና መከታ በነበረው ሠራዊት ላይ ጥቃት በመፈጸም ጁንታው ወራዳነቱን አሳይቷል። ይህ ድርጊቱም የትግራይን ህዝብ ባህልና ማንነት የማይገለጽና በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ አውሬያዊ ስብስብ ባህሪ ነው ያሉት አቶ የሺዋስ፤ ድርጊቱ በክርስትናም ሆነ በእስልምናም ነውርና የተወገዘ መሆኑንም አስረድተዋል። ከህዝብ ጋር ሆኖ አንበጣ ሲከላከል፣ የህዳሴ ግድብን ሲጠብቅ፤ ሰብል ሲሰበስብ፤ ከሌለው ላይ አዋጥቶ ትምህርት ቤት ሲያሰራ በነበረን የህዝብ ሠራዊት ከኋላው መውጋት ከከሃዲነትም በላይ መሆኑን ገልጸዋል። ቡድኑ የፈጸመው አስጸያፊ ድርጊት ኢትዮጵያንም ሆነ ፖለቲካውን ከአለማወቅ፣ ሃሳባቸውም ያረጀና ያፈጀ መሆኑን ካለመገንዘብ ነው ያሉት አቶ የሺዋስ፤ በመከላከያ ላይ የተሰራው ግፍ ሁሉም ኅብረተሰብ ከራስ ጸጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ ስሜቱ ዘልቆ የተሰማው መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህም በኮቪድ እና ህዳሴ ግድቡ ወቅት ካሳየው የአንድነት ስሜት በላቀ መልኩ የህወሓት ጁንታ ቡድን ህግ መጣሱን ተከትሎ መከላከያ በወሰደው ህግን የማስከበር እርምጃ እንደአንድ ሰው ስሜቱ መተሳሰሩን ተናግረዋል። የህብረተሰቡ አንድነት ደግሞ ለኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋ እንደመሆኑ በዚህ ረገድ ፓርቲዎችን፣ ሽማግሌዎችን፣ የኃይማኖት አባቶችን በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ህዝብ ሊመሰገን ይገባዋል፤ ብለዋል። እንደ አቶ የሺዋስ ገለጻ፤ ህግን ለማስከበርና ሀገርን ለማዳን መከላከያ የወሰደው እርምጃ ሌላም ተመሳሳይ ዕኩይ ባህሪ ላላቸው አካላት አስተማሪ ነው። ሀገር ከማዳኑም ባሻገር ኢትዮጵያ የምትኮራበት ተቋም መገንባት መቻሉንም ያመላከተ ነው። መከላከያ ሠራዊቱ በአጠቃላይ መከላከያ ተቋሙ ምን ያክል ጠንካራ እንደሆነ ያስገነዘበ፤ ከአየር ኃይሉ እስከ እግረኛው ድረስ ከአገር ውስጥ ላለው ቦርቧሪ ከውጭ ለሚያስበውም ወራሪ በጣም ጥሩ ትምህርት የሰጠ እና ጀግኖችን ያፈራ ሂደትም ሆኗል። አምባገነን ሁል ጊዜ ጠብ የሚጭረው ከወጣቱ ባሻገር እናቶችን፣ አረጋዊያንና በሽተኞችን ጭምር ለማስፈጀት ነው ያሉት አቶ የሺዋስ፤ እንደፓርቲ ደም በመለገስ ገንዘብ በመስጠት በምንችለው ሁሉ ከመከላከያ ጎን ቁመናል። ኅብረተሰቡም የሚችለውን ሁሉ ለመከላከያ ድጋፍ እያደረገ ነው። ይህ ድጋፍ እስከመጨረሻ ድረስ እንዲዘልቅ በማድረግ ሁሉም አጋርነቱን ሊያሳይ ይገባል ሲሉ አመልክተዋል። ‹‹ከመከላከያ ጎን ቆማችኋል ተብለው በገመድ ታንቀው የተገደሉ የትግራይ ልጆች አሉ። ይህ ሲታሰብ ያለአግባብ የተከፈለው መስዋትነት በጣም ብዙና ያሚያም ነው” ያሉት አቶ የሺዋስ፤ ፖለቲካ ማወቅ ዓለማወቅ፣ ህዝብ ይቅርታ መቀበል አለመቀበል ሌላ ነገር ሆኖ በተለይ በሰሜን ዕዝ ላይ የፈጸሙት አረመኔያዊ ተግባር ፈጽሞ ከሰውነት የወጡ ከትግራይ ህዝብ ጋር የማይተዋወቁ ከሌላ ዓለም የመጡ ፍጡራን ናቸው እንድንል አድርጎናል ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እኩይ ቡድን ለፍርድ እስኪቀርብ ድረስም ሁሉም ኢትጵያ ህዝብ ከመከላከያና ከጸጥታ አካላት ጎን እንዲቆምም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37692
[ { "passage": "መግለጫው በዋነኛነት ያተኮረው ከሰሞኑ የታሠሩበት አባላቱን ኤልያስ ገብሩና ስንታየሁ ቸኮል ላይ ሲሆን፤ ከአንድ ዓመት በፊት እስረኞች ተፈተው የነበረው ሁኔታ ወደ ኋላ እንደተቀለበሰም እስክንድር ተናግሯል።\n\n• \"ከጄ/ል አሳምነው ጋ በምንም ጉዳይ ያወራሁበት አጋጣሚ የለም\" እስክንድር ነጋ\n\n• \"ታከለ ኡማ አዲስ አበባን መምራት የለባቸውም\" እስክንድር ነጋ\n\n\"እስር ቤቶቻችን የህሊና እስረኞች አልባ የነበሩ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን የህሊና እስረኞች ያሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤ እነዚህም እስረኞች ኢ- ሰብአዊ በሆነ ሁኔታ ነው የተያዙት፤ ይህንንም መግለጫ ስንጠራ ያሉበትን ሁኔታ ለማሳወቅ እንዲሁም ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ለመጠየቅ ነው\" ብሏል። \n\nመግለጫው ተጀምሮ ለምን ያህል ደቂቃ ተሰጥቶ እንደነበር በትክክል እንደማያውቅ ለቢቢሲ ገልጾ፤ መግለጫው ተነቦ ጋዜጠኞች ሁለት ጥያቄ ጠይቀው መልስ መስጠት ሲጀምሩ እንደተቋረጠ ተናግሯል። \n\nመግለጫው ለመቋረጥ የበቃው \"ጥያቄ አለን\" በሚሉ ሰዎች በተነሳ ረብሻ ሲሆን፤ በባላደራው ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ላይ የተገኙ በቁጥር 10 የሚሆኑ ወጣቶች ደምፃቸውን ከፍ አድርገው ''ባንዲራችን ይህ ነው'' በማለት ባለ ኮከቡን የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ከፍ አድርገው ሲያሳዩ ነበር። \n\n''አገር መገንባት ነው የምንፈልገው አንጂ ማፍረስ አይደለም''፣ ''አይሳካልህም''፣ ''ምክር ቤቱ ኦሮሞን ያገለለ ነው''፣ ''ታከለ [የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ] መጤ አይደለም''፣ ''አዲስ አበባ የሁሉም ናት'' የሚሉ መፈክሮችን ደጋግመው ሲያሰሙ ነበር። \n\nየነበረውን ሁኔታ አረጋግቶ መቀጠል አይቻልም ነበር ወይ? በሚል ከቢቢሲ ለቀረበለት ጥያቄ \"ማረጋጋት አይቻልም\" የሚል ምላሽ የሰጠው እስክንድር፤ የታቀደበት እንደነበርና የተደራጀም እንደነበር ገልጿል።\n\n\"ሰንደቅ አላማዎቹ በደንብ ተዘጋጅተው፣ ጥቃት የሚያደርሱበት ስውር መሣሪያዎች ይዘው፤ የሚናገሩት ነገር በስሜት ሳይሆን በደንብ የተጠና እንደነበር የሚያመላክቱ ነገሮች አግኝተናል\" ብሏል።\n\nነገሮችን ለማረጋጋትና ሁኔታው ወደ ሌላ ከማምራቱም በፊት ቶሎ ከአዳራሹ እንደወጣም ይናገራል።\n\n• “የመከላከያው በአደባባይ ሚዲዎችን እከሳለሁ ማለት አስፈሪ ነው” ዶ/ር አብዲሳ ዘርዓይ\n\n• ለባለስልጣናቱ ግድያ አዴፓ ራሱን ተጠያቂ እንዲያደርግ ህወሐት ጠየቀ\n\n\"የምናዝነው ከመልዕክቱ ይልቅ የተፈጠረው ነገር በመጉላቱ ነው፤ የተነሳንበትን ዋነኛ አላማ ውጦብናል፤ በዚህም በጣም እናዝናለን\" ብሏል። \n\nመግለጫውን ከመስጠታቸው ከአንድ ቀን በፊት \"የተለመዱ\" የሚላቸው ማስፈራሪያዎችና ዛቻዎች እንደነበሩ የሚናገረው እስክንድር በስልክ፣ በቪዲዮም ማስፈራሪያ እንደደረሰው ገልጿል።\n\nጥዋት ላይም ቢሮ ሊገባ በነበረበት ወቅት 'ሲቪል የለበሰ' አንድ ፖሊስ ቢሮ ላይ ጠብቆ እንዳይገባ ከልክሎት እንደገፈተረው ለቢቢሲ ተናግሯል። \n\nከዚህም በተጨማሪ ጋዜጠኞች እንዳይገቡ እንደተከለከሉና የምክር ቤቱ አባል ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉና ሌላ አንድ አባል በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው እንደነበር ግን ብዙም ሳይቆይ እንደተለቀቁ ገልጿል።\n\nበተደጋጋሚ የባልደራስ ምክር ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት ሲዘጋጅ የተሰረዘበትን እስክንድር የፖለቲካ ምህዳሩ ስለመጥበቡ አንድ \"ቁንፅል ማሳያ\" ነው ይላል።\n\nከዚህ በላይ ግን ሰሞኑን አገሪቱ ውስጥ ከተከሰቱ ችግሮች ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በፀረ-ሽብር ሕግ መጠየቃቸው \"ግዙፋ ማሳያ\" እንደሆነም ይናገራል። \n\n\"አገራችን ወደ ኋላ እየተጓዘች ስለ መሆኗ፤ የተገባው ዲሞክራሲ፣ ይመጣል ተብሎ የተገባው ቃል ለመታጠፉ ምንም ማስረጃ የለም፤ ያ ትልቅ ማስረጃ ነው\" ብሏል።\n\nአክሎም \"በአጠቃላይ አገራችን ጥሩ አቅጣጫ ላይ አይደለም። ነገር ግን... ", "passage_id": "f9eefee901d3d4708c101e84fcd188b7" }, { "passage": "የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ባለፈው ማክሰኞ በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ሰላማዊና ህጋዊ ተቃውሞ ለማድረግ ስለሚቻል፣ በአንድ ወር ውስጥ አመራሩ ወደ አገር እንደሚመለስ አስታውቋል።ይህን ማስታወቂያ ይዘን አድማጮች ለድርጅቱ ያላቸውን ጥያቄ ለአመራሩ እንዲያቀር መድረክ ከፍተናል።የንቅናቄው ዋና ጸኃፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ዛሬ ከሚመልሱት ጥያቄ መካከል ንቅናቄው ወደ ፓርቲነት ይለወጣልን? ከሌሎቹ ፓርቲዎች ጋር ይዋሃዳልን? የሚሉትና ሌሎችም ይገኙባቸዋል።። ", "passage_id": "e4875b648074059a861e2a4ab3b41e9b" }, { "passage": " “የክልላችንን ፕሬዚዳንት ጨምሮ ከፍተኛ ባለስልጣናት የመገደላቸውን ዜና ከሰማሁ በኋላ ስጋት አድሮብኝ ነበር፡፡ከተማዋም ሆነች ክልሉ በአጭር ጊዜ ይረጋጋል የሚል እምነት አልነበረኝም፡፡ጦርነት የሚከሰት መስሎኝ ነበር፡፡ ነገር ግን እንደፈራሁት አልሆነም፡፡በአሁኑ ወቅት ከተማዋም ሆነ ክልሉ ሰላም የሰፈነበት ነው” ሲል ያብራረው የባህርዳር ከተማ ነዋሪ ወጣት ዮሴፍ ተስፋዬ ነው፡፡ ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም ከአማራ ክልል መዲና ባህርዳር የተሰማው ዜና እጅግ ዘግናኝ ነበር፡፡ የአማራ ክልል አስተዳዳሪ ዶክተር አምባቸው መኮንንን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ባለስልጣናት ላይ በተፈጸመባቸው ጥቃት ህይወታቸው ማለፉ የሚታወስ ነው፡፡ከተማዋ ክልሉ እንዲሁም ሀገሪቱ ወደ አስከፊ ሁኔታ እንዳትሸጋገር በሚል በርካቶች ስጋታቸውን ሲገልጹ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት ከተማዋ ስላለችበት ሁኔታ አስተያየታቸውን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከሰጡት የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወጣት ዮሴፍ አንዱ ነው፡፡ከጓደኞቹ ጋር በእግር በመጓዝ ላይ ሆኖ ነበር የተኩስ ድምፅ የሰመው፡፡የተኩስ ልውውጡ እየበረከተ ሲመጣ ግን ወደ ቤቱ አቅንቶ ቴሌቪዥን እንደከፈተ እና በቴሌቪዥን መስኮት ሲተላለፍ ነበረው ዜናም እጅግ እንዳስደነገጠው ይናገራል፡፡ “ዜናውን ስሰማ ከተማዋ የጦርነት አውድማ ሆና መቅረቷ ነው የሚል ስጋት አድሮብኝ ነበር፤ ከተማዋ በአጭር ጊዜ ወደ ሰላሟ በመመለሷ እጅግ ደስተኛ ነኝ፤ ከተማዋ ወደ ሰላሟ ልትመለስ የቻለችው የመንግሥት ጸጥታ ኃይልና የከተማዋ ህዝብ ባደረገው ጥረት ነው፡፡ይህም የከተማዋን ህዝብ ሰላም ወዳድነትና ስልጡንነት አመላካች ነው” ሲልም አስተያየቱን ሰጥቶናል ወጣት ዮሴፍ፡፡ የሆቴል ባለሙያው አቶ እስቲበል ደርሶ በበኩላቸው፤ ችግሩ ከተከሰተበት ዕለት አንስቶ ስለባህርዳር ከተማ ሲወራ የነበረው ከእውነታው የራቀ ነበር ይላሉ፡፡በጥቃቱ ማግስት በእግራቸው በመዟዟር ከተማዋን መቃኘታቸውንና ህዝቡ ኀዘንና ቁጭት ውስጥ መሆኑን ከሚያሳዩ አንዳንድ ስሜቶች በዘለለ ከተማዋ እጅግ ሰላማዊ እንደነበረች ተናግረዋል፡፡“ሁሉም ዓይነት እንቅስቃሴዎች ነበሩ፡፡የግልና የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ተቋማትም አገልግሎታቸውን ሲሰጡ ነበር” ብለዋል፡፡ “ህዝቡ በአሉባልታዎች ባለመነዳት፣ ራሱንና አካባቢውን ነቅቶ መጠበቅ በመቻሉ የከተማችን ሰላም አልደፈረሰም” የሚሉት አቶ እስቲበል፤ በጥቃቱ ዙሪያ ግልጽ ያልሆኑን እርስ በእርሳቸው የሚጣረሱ መረጃዎች በህዝብና በመንግሥት መካከል የነበረው መተማመን እንዲደፈርስ አድርጓል ብለዋል፡፡ይህም ህዝቡን ለውዥንብር መዳረጉንና አሁንም ቢሆን በጉዳዩ ዙሪያ ግልጽ የሆኑ መረጃዎች ለህዝቡ ሊደርሱ ይገባል ብለዋል፡፡ ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ፋርማሲስት ፈለገወርቅ አሰፋ በበኩላቸው፤ ግልጸኝነት የሌለበትና በሃሳብ የበላይነት ላይ ያልተመሰረተ ፖለቲካ ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ ትልቅ ሥራ ይሠራሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸውን የህዝብ መሪዎች እንዲቀጠፉ አድርጓል፡፡ሀገሪቷ ውድ መሪዎቿን እንድታጣም ምክንያት ሆኗል፡፡ዳግም መሰል ችግር እንዳይፈጠር ግልጽነትና በሃሳብ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ ማራመድ ያስፈልጋል ይላሉ፡፡ እንደ ፈለገወርቅ ገለጻ፤ በተለይም ለህዝብ ጥቅም የሚሠሩ አመራሮች ግልጸኝነት የተሞላበት ፖለቲካ በማካሄድ ለህዝቡ አርዓያ ሊሆኑ ይገባል፡፡መንግሥት የሚያደርገው እንቅስቃሴ ብቻውን ችግሮችን አይቀርፍም፡፡ህዝቡ ለራሱ ብቻ ከማሰብ ወጥቶ ለሀገር አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበት ማሰብ ይጠበቅበታል፡፡ለሀገር ያለውን ፍቅር በቃል ብቻ ከመግለጽ ወጥቶ በተግባር ማሳየት አለበት፡፡ በከተማዋ በሹፍርና ሙያ የሚተዳደሩት አቶ ፈቃደሥላሴ እሸቱ በበኩላቸው እንደገለጹት መንግሥት የህግ የበላይነት በማስከበር ረገድ ድክመቶች ይታዩበታል፡፡መንግሥት የህግ የበላይነትን ለማስከበር ምንም ሊያመነታ አይገባም፡፡ መብት ነው ተብሎ ሁሉም ነገር ልቅ መደረጉ ሀገሪቷን ዋጋ እያስከፈላት ነው፡ ፡የህዝቡን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ የሚሠሩ ሥራዎች ሳይሠሩ ሁሉንም ነገሮች ልቅ ማድረግ ተገቢ አይደለም፡፡ መንግሥት ህግን የማስከበር ተግባሩን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል፡፡መንግሥት ህግ ማስከበር ላይ ያለውን ውስንነቶች ማስተካከል ከቻለ ብዙ ችግሮችን መቅረፍ ይቻላል ይላሉ፡፡ አቶ ፈቃደሥላሴ\nእንደሚሉት መንግሥት ሀሉንም\nነገር የሚያይ ዓይንና\nየሚሰማ ጆሮ ሊኖረው\nአይችልም፡፡በመሆኑም መንግሥት\nሰላምን ለማስከበር የሚያደርገውን\nጥረት ህዝቡ ሊያግዝ\nይገባል፡፡መንግሥት ማስተካከል\nያለበትን ነገሮች ማስተካከል\nየሚችለው ከህብረተሰቡ በሚሰጥ\nጥቆማና አስተያየት ነው፡\n፡ለሰላም ጸር የሚሆኑ\nእንቅስቃሴዎች ሲኖሩ ለፖሊስና\nለጸጥታ አካላት በመጠቆም\nየበኩሉን ሊወጣ ይገባል፡፡\n አዲስ ዘመን ሐምሌ 15/2011 ", "passage_id": "c3d0d6f8043d3e4006e9f2d914cb8037" }, { "passage": "«ምርጫ\nቦርድ ሊያዘን አይችልም» – የኢዜማ ምክትል ሊቀመንበር ዶክተር ጫኔ ከበደአዲስ\nአበባ፡- የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) መመስረቱን የማሳወቅ ሂደት እንዳልተተገበረ፤ መሰረትን ያሉት ፓርቲዎችም መክሰማቸውን በተመለከተ ፓርቲዎቹ እንዳላሳወቁ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለፀ፡፡ ‹‹ምርጫ\nቦርድ ሊያዘን አይችልም፤ ፓርቲዎች በራሳቸው መተዳደሪያ ደንብ በጠቅላላ ጉባኤያቸው ወስነው አዲሱን ፓርቲ ለመመስረት ፈቃደኛ ሆነው ሪፖርት በማቅረባቸው ፓርቲው አዲስ ሆኖ እንዲቋቋም ተደርጓል›› ሲል ኢዜማ አስታውቋል፡፡የብሔራዊ\nምርጫ ቦርድ የኮሙኒኬሽን አማካሪ ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል እንደገለፁት፤ በመገናኛ ብዙሃን የተገለፁት ራሳቸውን አክሰመው አንድ ፓርቲ ለመመስረት ተሰባስበዋል የተባሉት የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአርበኞች ግንቦት 7፣ ሰማያዊ ፓርቲ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲና የጋምቤላ ክልላዊ ንቅናቄ ከስመው ወደ ኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ተጠቃልለዋል ቢባልም አንድም ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ ከስሜያለሁ ብሎ አላሳወቀም፡፡ አዲሱ\nየኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ መቋቋሙ በመገናኛ ብዙሃን ቢገለፅም፣ ከቦርዱ ፓርቲውን ለማቋቋምና አባላትን ለመመዝገብ ያመች ዘንድ ህጋዊ ደብዳቤ እንዲሰጣቸው ከመጠየቅ ውጭ እስከአሁን በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳልተመዘገበ አማካሪዋ ተናግረዋል፡፡ የኢዜማ ምክትል ሊቀመንበር ዶክተር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው ፓርቲዎች በራሳቸው መተዳደሪያ ደንብ በጠቅላላ ጉባኤያቸው ወስነው አዲሱን ፓርቲ ለመመስረት ፈቃደኛ ሆነው ሪፖርት በማቅረባቸው ከወረዳ ጀምሮ አባላትን በማዋሃድ ፓርቲው አዲስ ሆኖ እንዲቋቋም ተደርጓል፤ ምርጫ ቦርድ ሊያዝዘን አይችልም፤ ከአሁን በኋላ አባላት የሰማያዊ፣ የኢዴፓ… ተብለው ሳይከፋፈሉ ሁሉም የኢዜማ አባል ሆነው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡ ዶክተር\nጫኔ ኢዜማ የመንግሥት ሥራ ውስጥ የፓርቲ ጣልቃ ገብነት እንዳይኖር እንደሚከላከል፤ በኢዜማ በኩል የፓርቲው ሊቀመንበር የፓርቲ ሥራውን ሲሠራ፤ የፓርቲው መሪ ደግሞ መንግሥታዊ የሆኑ ሥራዎችን በማከናወን ፓርቲ እና መንግሥት ተነጣጥለው የሚሠሩ መሆናቸውን ገልፀው፤ ይህ በሌላው ዓለምም የተለመደ ስለሆነ ትክክለኛ አካሄድ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ‹‹ ህዝብን\nግራ በማያጋባ መልኩ የመንግሥት አደረጃጀት እና የፖለቲካ አደረጃጀት ቁልጭ ብሎ መታወቅ አለበት›› ያሉት ዶክተር ጫኔ፤ ይህንን የፓርቲውን አደረጃጀት በፓርቲያቸው በኩል በወረዳ ደረጃ ሳይቀር እንደዘረጉት አሳውቀዋል፡፡ ተግባሩ የመንግሥት አሠራር በፓርቲ ተፅዕኖ ውስጥ እንዳይገባ ነፃና ገለልተኛ የሲቪል ሰርቪስ መዋቅር እንዲኖር ታስቦ የተሠራ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ አዲስ ዘመን ግንቦት 16/2011ምህረት\nሞገስ", "passage_id": "5ee72ba10dca433caffe2b475ac29697" }, { "passage": "ሃያ ስምንት እንደሚሆኑ አብን ያሳወቃቸው አባላትና ደጋፊዎቹ የታሠሩት የመሪዎቻቸውን ጉዳይ ለመከታተል አዲስ አበባ፤ አራዳ ምድብ ችሎት ተገኝተው በነበረ ጊዜ መሆኑንም አብን ገልጿል።“የታሠሩብን ‘አማራነት እና እውነት አይታሰርም’ የሚል ሸሚዝ የለበሱ ናቸው” ሲሉ የንቅናቄው የፅሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ በለጠ ካሣ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።የተያዙት ሰዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የሦስት ሺህ ብር ዋስ እንዲያቀርቡ መጠየቃቸውንም አቶ በለጠ አመልክተዋል። ", "passage_id": "5836b6232e798449bdace20c0c952caa" } ]
ec6cd04a810eeb8f5e102836d9b15fa0
ede1323482ee788e2a68c8b3000627ca
የቮሊ ቦል ፕሪሚየር ሊግ ከ2ሳምንት በኋላ ይጀመራል
 የሀበሻ ሲሚንቶ የቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመቱን ከሁለት ሳምንት በኋላ የሚጀምር ይሆናል፡፡ በ2011 ዓ.ም የሊጉ አፈጻጸምም ግምገማ መሰረትም የተሻለ የውድድር ዓመት እንደነበረም ተመልክቷል፡፡ በዘጠኝ ክለቦች መካከል የሚካሄደው የ2012 ዓ.ም የሀበሻ ሲሚንቶ የፕሪሚየር ሊግ ውድድር መርሃ ግብሩን በሁለት ሳምንታት ውስጥ የሚጀምር መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በድረ-ገጹ አስነብቧል፡፡ ፌዴሬሽኑ የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ያከናወነ ሲሆን፤ ያለፈውን የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ደረጃ መነሻ በማድረግም የመጀመሪያ ዙር የውድድር መርሀ ግብር ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡ በዚህም መሰረት ወላይታ ድቻ ከውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን፣ መደወላባ ዩኒቨርስቲ ከፌደራል ማረሚያ ቤት፣ ሙገር ሲሚንቶ ከጣና ባህርዳር እንዲሁም አዲስ አበባ ፖሊስ ከመከላከያ እንደሚገናኙ ታውቋል ፡፡ ፌዴሬሽኑ የ2011 ዓ.ም የሀበሻ ሲሚንቶ የወንዶች የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይ ግምገማ ያካሄደ ሲሆን፤ በግምገማውም የክለብ አመራሮች፣ የዳኞች ኮሚቴ፣ የቴክኒክ ኮሚቴ እና የውድድርና ስነ ስርዓት ኮሚቴዎች ተሳትፈዋል፡፡ ፌዴሬሽኑ በ 2 ዙር በአራት ከተሞች ባካሄዳቸው ውድድሮች ላይ የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞችንና ክፍተቶችን በመለየት የመከረ ሲሆን፤ የፕሪሚየር ሊጉ ውድድር ወቅቱን ጠብቆ መጠናቀቅ፣ ጠንካራ የፕሪሚየር ሊግ ፉክክር መታየት፣ የኮኮቦች ምርጫ ያለምንም ቅሬታ መካሄድ እና አንፃራዊ የስፖርታዊ ጨዋነት መስፈን በጥንካሬ ከተነሱ ነጥቦች መካከል ተጠቃሾቹ ናቸው ፡፡ ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር የ2011 የሀበሻ ሲሚንቶ ፕሪሚየር ሊግ የተሻለ ውድድር የተካሄደበትም ነው፡፡ ነገር ግን በዳኞች የሚታዩ የዳኝነት ክፍተቶች፣ ከሜዳ ውጪ የሚታዩ የስፖርታዊ ጨዋነት ጉድለቶች፣ አሰልጣኞች በውድድር ሜዳ የሚያሳዩት ያልተገባ ስነ-ምግባር፣ የውድድር ኮሚሽነሮች የተሟላ ሪፖርት ያለ ማቅረብ፣ በአንዳንድ ተጨዋቾች የሚታዩ የስነ-ምግባር ጉድለቶች፣ ውጤትን በፀጋ ያለመቀበል እና ክለቦች ለውድድር ቅድመ ዝግጅት ባለማድረግ ችግሮች እንደነበሩበት በተሳታፊዎች ተነስቷል፡፡ በአዲሱ የፕሪሚየር ሊግ ዓመት እንዳይደገሙም የመፍተሄ አቅጣጫ ተቀምጧል ፡፡ ፌዴሬሽኑ ከግምገማ እና እጣ ማውጣት ስነ- ስርዓት በኋላ በውድድሩ ለሚሳተፉ ክለቦች የቁሳቁስ ድጋፍ ማበርከቱንም በዘገባው ተጠቁሟል፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 17/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=23241
[ { "passage": "በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወልድያ ከፕሪሚየር ሊጉ መውረዱን ሲያረጋግጥ ሙገር ሲሚንቶም የወልድያን እግር ሊከተል ተቃርቧል፡፡መልካ ቆሌ ላይ አርባምንጭ ከነማን ያስተናገደው ወልድያ 1-0 ተሸንፏል፡፡ ሽንፈቱን ተከትሎም 3 ጨዋታ እየቀረው 12ኛ ደረጃ ላይ ካለው ኤሌክትሪክ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት 12 በመድረሱ ባለፈው አመት ወደነበረበት ብሄራዊ ሊግ መውረዱን አረጋግጧል፡፡አሰላ ላይ አዳማ ከነማን ያስተናገደው ሙገር ሲሚንቶ 1-1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቶ ከኤሌክትሪክ ጋር የነበረውን ልዩነት የማጥበብ እድሉን አበላሽቷል፡፡ ሙገር 12ኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው ኤሌክትሪክ ጋር ያለው የነጥ ልዩነት 4 ሆኗል፡፡ይርጋለም ላይ መከላከያን ያስተናገደው ሲዳማ ቡና 0-0 አቻ ተለያይቶ ለዋንጫ የነበረው ተስፋ አክትሟል፡፡ ሲዳማ ቡና የሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ሶስቱንም ጨዋታ አሸንፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሶስቱንም ጨዋታ መሸነፍ ይኖርበታል፡፡አዲስ አበባ ስታድየም ላይ ወላይታ ድቻን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ቡና 0-0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል፡፡ ኢትዮጵያ ቡና በአንዋር ያሲን እየተመራ የመጀመርያ ነጥቡን ሲያገኝ ከ5 ተከታታይ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ ያገኘው የመጀመርያ ነጥብ ሆኗል፡፡ኤሌክትሪክ 0-4 ደደቢትኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1-1 ሀዋሳ ከነማዳሽን ቢራ 1-2 ቅዱስ ጊዮርጊስሲዳ ቡና 0-0 መከላከያሙገር ሲሚንቶ 1-1 አዳማ ከነማወልድያ 0-1 አርባምንጭ ከነማኢትዮጵያ ቡና 0-0 ወላይታ ድቻ", "passage_id": "089502c05a1e7248ead1bfba67248c88" }, { "passage": "የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፈዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አባላት ምርጫ እየተካሄደ ነው።በአትሌቲክሱ ሩጫ ስፖርት ዜና ፈይሣ ሌሊሣ በሂዊስተን ግማሽ ማራቶን በሁለተኝነት አጠናቀቀ።11ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ግጥሚያዎች እየተካሄዱ ነው።ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። ", "passage_id": "644d6107bf160c6dbf4a6c93b5c38c68" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በይፋ በአዲስ አበባ ስታድየም ተጀምሯል፡፡ በመክፈቻው እለት በተደረጉ ጨዋታዎችም ደደቢት እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል፡፡በ9፡00 መከላከያን የገጠመው ኤሌክትሪክ 1-0 በማሸነፍ የውድድር ዘመኑን በድል ከፍቷል፡፡ የኤሌክትሪክን የድል ግብ ናይጄርያዊው አጥቂ ፒተር ኑዋድኬ በ40ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል፡፡በ11፡30 ደደቢት ወላይታ ድቻን አስተናግዶ 2-1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ደደቢት በ9ኛው ደቂቃ ሳምሶን ጥላሁን ባስቆጠረው የቅጣት ምት ግብ ቀዳሚ ሲሆን ወላይታ ድቻዎች በ61ኛው ደቂቃ ያገኙትን የፍፁም ቅጣት ምት ኃይለየሱስ ብርሃኑ ወደ ግብነት ቀይሮ አቻ ሆነዋል፡፡ የደደቢት የማሸነፍያ ግብ የተገኘችው በ80ኛው ደቂቃ በሳሙኤል ሳኑሚ የፍፁም ቅጣት ምት ግብ አማካኝነት ነው፡፡የፕሪሚየር ሊጉ አንደኛ ሳምንት ቀሪ 5 ጨዋታዎች ነገ ይደረጋሉ፡፡ የአምናው ቻምፒዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አዳማ አቅንቶ አዳማ ከነማን ይገጥማል፡፡ የአዲስ አበባ አምበር ዋንጫ አሸናፊው ዳሽን ቢራ ዘንድሮ ያደገው ድሬዳዋ ከነማን ያስተናግዳል፡፡ በሲዳማ ደርቢ የሀዋሳ ሱንትራል ዋንጫ አሸናፊው ሀዋሳ ከነማ ሲዳማ ቡናን ያስተናግዳል፡፡ አዲስ መጪው ሀዲያ ሆሳእና ደግሞ አርባምንጭን ይጎበኛል፡፡ ሁሉም ጨዋታዎች 9፡00 ላይ የሚጀምሩ ሲሆን 11፡30 አዲስ አበባ ስታድየም ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚያደርጉት ጨዋታ የአንደኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ይሆናል፡፡", "passage_id": "318ff14e22fcc30e7e13d8a4ffcad324" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዓለማችን ላይ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተ ወዲህ በርካታ ታላላቅ የሊግ ውድድሮች መቋረጣቸው ይታወቃል።የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ከተቋረጡ የሊግ ውድድሮች ውስጥ አንዱ የሆነው የጀርመን ቡንደስሊጋ በቅርቡ ወደ ውድድር ለመመለስ ፍላጎት እንዳለው የጀርመን እግር ኳስ ሊግ አስታውቋል።ቡንደስሊጋው የፊታችን ግንቦት 1 ወደ ውድድር በመመለስ ያለ ተመልካች ውድድሮቹን አድርጎ ለማጠናቀቅ ዝግጁ መሆኑን የእግር ኳስ ሊጉ ገልጿል።ቡንደስሊጋውን እና የሁለተኛ ዲቪዥን ጨዋታዎችን የሚያስተዳደረው የጀርመን እግር ኳስ ሊግ በዛሬው እለት ከ36 ፕሮፌሽናል ክለቦች ጋር ከተወያየ በኋላ ነው የዘንድሮውን የውድድር ዓመት ያለተመልካች የመጨረስ ፍላጎት እንዳለው የገለፀው።ሆኖም ግን በሀገሪቱ የሰዎች እንቅስቃሴ በተገደደበት በዚህ ወቅት የጀርመን እግር ኳስ ሊግ አስተዳዳሪዎች ፍቃድ ያገኛሉ የሚለው ጥያቄ ሆኗል።የጀርመን እግር ኳስ ሊግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ክርስቲያን ሲፈርት “ግንቦት ወር ውድድር ለመጀመር ዘግጅ ነን፤ የሚራዘም ከሆነም ለዚያም እንዘጋጃለን” ብለዋል።የጀርመን መንግስት የኮሮናቫይረስን ለመቆጣጠር በሚል ብዙ ሰው የሚሰበሰብበት ሁነት እስከ ነሀሴ ወር መጨራሻ እንደማይኖር ማስታወቁ ይታወሳል።ምንጭ፦ ቢቢሲ", "passage_id": "09df2e8bf3614cac5e75ea806365fac6" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣መስከረም 26 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የኢትዮጵያ የወንዶች እግር ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ታህሳስ 3 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሸር ካምፓኒ ይፋ አድርጓል።የፕሪሚየር ሊግ ሸር ካምፓኒው በኮቪድ ውስጥ ሆኖ የኢትጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን ለማስጀር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የቅደመ ዝግጅት ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑንም አስታውቋል።በዚህም ዝግጅቱን መሠረት በማድረግ የፕሪሚየር ሊግ ውድድሩ ታህሳስ 03 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚጀመር ለተሳታፊ ክለቦች ማሳወቁን ከኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።\nየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "9203596f578fb2ef8b7709f210370060" } ]
26aeefc34a61ca72be39763d1b900eb1
b8f747ad91eee20d11655405f6d3ca4d
ከሽንፈት ማግስት የሚደረጉት ወሳኝ የብሔራዊ ቡድን ፍልሚያዎች
ባለፈው ቅዳሜና ዕሁድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኖች በሁለቱም ፆታ ያደረጓቸውን ጨዋታዎች በሽንፈት ማጠናቀቃቸው ይታወሳል። የወንዶች ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ ቅዳሜ ዕለት ለ2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድባቸውን የመጀመሪያ ጨዋታ ከሜዳቸው ውጪ አድርገው በማዳጋስካር አንድ ለምንም መሸነፋቸው ይታወሳል። የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ሉሲዎቹ ደግሞ በመካከለኛውና ምሥራቅ አፍሪካ(ሴካፋ) ዋንጫ ዕሁድ ዕለት የምድባቸውን የመጀመሪያ ጨዋታ አድርገው በኬንያ ሁለት ለዜሮ ተረተዋል። ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች ዛሬ ከሽንፈታቸው ማግስት ወሳኝ ፍልሚያ የሚጠብቃቸው ይሆናል። በኬኒያ አቻቸው በሁለት ደቂቃ ውስጥ ሁለት ግብ አስተናግደው የተሸነፉት ሉሲዎቹ ከምድባቸው ለማለፍ ዛሬ ከዩጋንዳ ጋር የሚያደርጉት ወሳኝ ጨዋታ ይጠብቃቸዋል። አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው በዛሬው ጨዋታ መጠነኛ የተጫዋች ለውጥ እንደሚኖር ጠቅሰው፤ የሚችሉትን ሁሉ ሜዳላይ ለማድረግ ተጫዋቾቹ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ‹‹ተጫዋቾቹ ምንም የሚፈረድባቸው ነገር የለም፣ በርካታ ወራት አርፈው ነው የመጡት፣ ክለቦቻችን ዕረፍት ላይ ስለነበሩ የዝግጅት ጊዜ አልነበራቸውም፣ የኔ እና የተጫዋቾቼ ህልማችን በ2020 ብሔራዊ ቡድኑን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማሳለፍ ነው፣ ይህ ውድድር ደግሞ እንደ ዝግጅት ይጠቅመናል፣ ብናሸንፍም ጮቤ አንረግጥም ምክንያቱም አልሠራንም፣ ነገር ግን ያለንን ጊዜ በመጠቀም ህልማችንን እናሳካለን፣ ይህን ማድረግ ካልቻልን መጠየቅ ያለብኝ እኔ እንጂ ተጫዋቾቼ አይደሉም፣ ዝግጅት ሳይሠሩ ውጤት መጠበቅ እንጀራ ሳያዘጋጁ ወጥ አቅርቦ ምሳ እንብላ እንደማለት ነው፣ ስለዚህ ከዚህ ውድድር ብዙ እንማራለን ለአፍሪካ ዋንጫው ሠርተን ለማለፍ እንጥራለን›› በማለት ለሽንፈቱ ኃላፊነቱን እንደወሰዱ በስፍራው ለሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። በታንዛኒያ አዘጋጅነት የሚካሄደው የሴቶች ሴካፋ ዋንጫ ኢትዮጵያ ከኬንያ፣ ዩጋንዳና ጅቡቲ ጋር መደልደሏ ይታወቃል። ሉሲዎቹ የመጀመሪያውን ጨዋታ መሸነፋቸውን ተከትሎ ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ ያላቸውን ተስፋ የሚያለመልሙት ዛሬ ከዩጋንዳ ጋር በሚኖራቸው ወሳኝ ፍልሚያ ይሆናል። ይህን ጨዋታ በሽንፈት ደምድመው በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ጅቡቲን ቢያሸንፉ እንኳን ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋ አይኖራቸውም። የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ የግድ ቢሆንም በአቻ ውጤት መለያየት ከቻሉ የሌሎቹን ውጤት ጠብቀው ወደ ቀጣይ ዙር የማለፍ ተስፋቸውን ሊያለመልሙ ይገደዳሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ በ2021 በካሜሩን አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ ከማዳጋስካር ጋር ከሜዳው ውጪ አድርጎ በ 1 ለ 0 ውጤት መሸነፉ ይታወቃል።ዋልያዎቹ በጨዋታው የታዩባቸውን በተለይም ኳስን ከመረብ የሚያገናኝ ጨራሽ አጥቂ ክፍተቶች ለመሸፈን አልጣኝ አብርሃም መብራቱ በውጭ ያሉ ተውልደ ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾችን በቀጣይ ጨዋታዎች ለማካተት እንዳሰቡ ለመገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። አሰልጣኙ ‹‹በዛሬው ጨዋታ ቡድናችን ከሜዳ ውጪ ከዕረፍት በፊት በመከላከል ላይ ያተኮረ እንቅስቃሴ አድርጓል፣ ኳስን በመቆጣጠር ከዕረፍት መልስ በማጥቃት ላይ ያተኮረ እንቅስቃሴም አድርጓል›› ብለዋል።የማዳጋስካር ቡድን ከወራት በፊት በአፍሪካ ዋንጫ እነ ናይጄራያንና ኮንጎን አሸንፎ ግማሽ ፍፃሜ የደረሰ መሆኑን ያስታወሱት አሰልጣኙ ቡድናቸው 1ለ0 መሸነፉ መጥፎ የሚባል ውጤት እንዳልሆነ አብራርተዋል። በዋልያዎቹ ስብስብ አብዛኞቹ ተጫዋቾች አዲስ መሆናቸውን የጠቆሙት አሰልጣኝ አብረሃም በቀጣዩ ጨዋታ ክፍተቶችን እንደሚያርሙ ተናግረዋል። ‹‹የቡድኑን የአጥቂ ችግር ለመቅረፍ ከአገር ውስጥም ወይም ከውጭ ያሉትን በቀጣይ ጨዋታ እናካትታለን›› ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ዋልያዎቹ ከማዳጋስካሩ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ ጊዜ ሳያጠፉ ወደ ባህርዳር ያቀኑ ሲሆን ዛሬ ጠንካራዋን ኮትዲቯር የሚገጥሙ ይሆናል። ዋልያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫው ማጣሪያ ከኮትዲቯር፣ማዳጋስካርና ኒጀር ጋር መደልደሏ ይታወቃል። ኮትዲቯር ቅዳሜ ዕለት ከሜዳዋ ውጪ ኒጀርን ገጥማ አንድ ለዜሮ በሆነ ውጤት ማሸነፏ ይታወሳል። አዲስ ዘመን ህዳር 9 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22770
[ { "passage": "ለ2004 የአቴንስ ኦሊምፒክ ለማለፍ የመጨረሻው ምዕራፍ ደርሶ የነበረው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ብሔራዊ ቡድን ከታሪካዊው ውድድር የቀረበት ሁኔታ “የሞሮኮ ሴራ ነው” ሲል ቢንያም አሰፋ በትውስታ አምዳችን ይናገራል።ጊዜው 1996 ነው። ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ ማጣርያ ተሳትፎ ታሪኳ እንዲህ የመጨረሻ ምዕራፍ ደርሳ አታውቅም። በአሰልጣኝ ሥዩም አባተ የሚመራው ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ታዲዮስ ጌታቸው፣ ጌቱ ተሾመ፣ አንዷለም ንጉሴ (አቤጋ)፣ ኤልመዲን መሐመድ፣ ታፈሰ ተስፋዬ፣ ደብሮም ሐጎስ፣ ቢንያም አሰፋ እና ሌሎችም ነበሩ። ከሞሮኮ፣ አንጎላ እና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለችው ኢትዮጵያ በሜዳዋ ያደረገቻቸውን ሦስቱንም የምድብ ጨዋታዎች በሙሉ በማሸነፍ ዘጠኝ ነጥብ ብትሰበስብም ከሜዳዋ ውጭ ያደረገቻቸውን ጨዋታዎች በአንፃሩ በሙሉ ተሸንፋለች።የምድቡ የመጨረሻ ጨዋታዎች ወደ አቴንስ የሚወስደውን ትኬት የሚቆርጠውን ቡድን የሚወስኑ በመሆኑ ተጠባቂ አድርገውታል። ከመጨረሻው ጨዋታ በፊት አንጎላ በ10 ነጥብ ስትመራ፣ ኢትዮጵያ በ9 ትከተላለች፣ ሞሮኮ ደግሞ 8 ነጥቦች ይዛ ሦስተኛ ላይ ተቀምጣለች። ኢትዮጵያ ለማለፍ ካምፓላ ላይ ዩጋንዳን የማሸነፍ ግዴታ ውስጥ ስትገባ አንጎላ በሞሮኮ ነጥብ መጣል ይኖርባታል። አንጎላ በአንፃሩ ሞሮኮን ከሜዳዋ ውጪ ማሸነፍ በቀጥታ የማንንም ውጤት ሳትጠብቅ ወደ ኦሊምፒክ እንድታመራ ያደርጋታል። አጣብቂኝ ውስጥ የገባችው ሞሮኮ ደግሞ አንጎላን በሜዳዋ አሸንፋ የኢትዮጵያን ሽንፈት ትጠብቅ ነበር። ዩጋንዳ አነስተኛ ነጥብ ያላት በመሆኑ ከመርሐ ግብር ማሟያ ውጪ መሸነፍ ማሸነፍ ለእርሷ ምንም ፋይዳ የለውም።በዚህ ስሌት መሠረት በአሰልጣኝ ሥዩም አባተ የሚመራው ቡድን የማለፍ ተስፋውን ይዞ ወደ ካምፓላ ቢያቀናም ምንም የማለፍ ዕድል በሌላት ዩጋንዳ ሽንፈት አስተናግዶ እና ወደ አቴንስ ሳያመራ ቀርቷል። የወቅቱ የቡድኑ ተጫዋች የነበረው ቢንያም አሰፋም ጋር ጊዜውን ሲያስታውስ “የሞሮኮ ሴራ ነበር” ይላል።” በወቅቱ ጥሩ የሚባል ቡድን አሰልጣኝ ሥዩም አባተ ሰርቶ ነበር። የመጨረሻ ጨዋታውን ብናሸንፍ እናልፋለን። ዩጋንዳ ላይ እየተጫወትን እነርሱ ቀድመው ጎል ቢያስቆጥሩም እረፍት ከመውጣታችን በፊት አቻ ሆንን። የሚገርምህ ዩጋንዳዎች ቢያሸንፉ የማለፍ እድል የላቸውም፤ ሆኖም ጠንክረው ወጥረው ይዘውን ይጫወታሉ። በመሐል በመሐል እንጠይቃቸዋለን፤ ‘ምንድነው እንዲህ የምትሆኑት? አንድ የምስራቅ አፍሪካ ቡድን ቢያልፍ አይሻልም?’ እያልን እናወራቸው ነበር። ሆኖም ይባሱኑ በሁለተኛው አጋማሽ ጎል አግብተው ጨዋታው 2-1 ይጠናቀቅና ወደ አቴንስ የነበረን ጉዞ ይገታል። የማለፍ ዕድላችን ባለመሳካቱ አዝንን እኔ በግሌ በጣም ይቆጨኝ ነበር። ከጊዜ በኃላ የዩጋንዳ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የነበረው አሳኒ ባጆፔ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲመጣ ስለሁኔታው ጠየቅኹት። ‘ለምድነው እንደዛ ኃይለኛ የሆናችሁብን? በጣም ስትከላከሉ ነበር።’ ብዬ ስጠይቀው የመለሰልኝ መልስ “የሞሮኮ እግርኳስ ፌዴሬሽን ለዩጋንዳ ፌዴሬሽን ብር ከፍሏል” በማለት ለተጫዋቾቹ በነስ ወከፍ 500 ዶላር ተከፍሏቸው እንደነበር ነገረኝ። እኔም በጣም ገርሞኝ ለካ እንዲህ ያለ ነገርም አለ ብያለሁ። ”", "passage_id": "e7e18a75cc1ebbc74963f98d732a95c0" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአዲስ አበባ ስታዲየም ከዛምቢያ አቻው ጋር ያደረገውን የአቋም መፈተሻ ጨዋታ 3-1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።በኮቪድ-19 ምክንያት ወደ 2022 ለተሸጋገረው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የማጣሪያ ጨዋታዎች እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በህዳር ወር የመጀመሪያ ቀናት ከኒጀር ጋር ላለበት የምድቡ 3ኛ እና 4ኛ ጨዋታ ይረዳው ዘንድ በዛሬው ዕለት ሁለተኛ የአቋም መለኪያ ጨዋታውን ከዛምቢያ ጋር በአዲስ አበባ ስታዲየም አከናውኗል። በጨዋታውም ተጋባዦቹ ዛምቢያዎች እጅግ ከፍተኛ የጨዋታ ብልጫ በማሳየት ጨዋታውን 3-1 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።መስከረም 18 በተሠጠ ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ የዋሊያዎቹ ዋና አሠልጣኝ በመሆን የተሾሙት አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ከሀሙሱ የመጀመሪያ የአቋም መለኪያ ጨዋታ ስድስት ለውጦችን አድርገው ለጨዋታው ቀርበዋል። በዚህም አሠልጣኙ አቤል ማሞ፣ ሱሌማን ሀሚድ፣ አንተነህ ተስፋዬ፣ አስቻለው ታመነ፣ ኃይለሚካኤል አደፍርስ፣ ሀብታሙ ተከስተ፣ ታፈሰ ሰለሞን፣ ሱራፌል ዳኛቸው፣ አማኑኤል ገ/ሚካኤል፣ ሙጁብ ቃሲም እና አዲስ ግደይ በቋሚነት ተጠቅመው ጨዋታውን ጀምረዋል። በጨዋታውም ተጋባዦቹ ዛምቢያዎች በመጀመሪያው አጋማሽ ፍፁም የጨዋታ ብልጫ ሲይዙ ባለሜዳዎቹ ደግሞ በአንፃራዊነት በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታውን የሃይል ሚዛን ወደ ራሳቸው አድርገው ታይተዋል።ኳስን ከግብ ክልላቸው ጀምሮ መስርቶ ለመውጣት ሲጥሩ የነበሩት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች አብዛኞቹ ጥረቶቻቸው የተሳካ ቢመስሉም በተወሰኑ አጋጣሚዎች ግን ኳሱን በአደጋ ቀጠና እየተነጠቁ ራሳቸው ላይ አደጋን ሲጋብዙ ታይቷል። በዚህ እንቅስቃሴም በአስረኛው ደቂቃ ዛምቢያዎች ተጭነው በመጫወታቸው ያገኙትን ኳስ በጥሩ ቅንጅት ወደ ዋሊያዎቹ የግብ ክልል ይዘው በማምራት የመጀመሪያ ሙከራ አድርገዋል። ከአራት ደቂቃዎች በኋላም ሀብታሙ ተከስተ በመሐል ሜዳ የግራ ክፍል ለኃይለሚካኤል አደፍርስ ሊያቀብል የነበረውን ኳስ ኮሊንስ አቋርጦ በፍጥነት ወደ ፊት ያሳለፈውን ኳስ ኢማኑኤል ቻቡላ ከሳጥን ውስጥ የአቤል ማሞን አቋቋም ተመልክቶ በቀላሉ ቀዳሚዋን ጎል ለቡድኑ አስቆጥሯል።ከኳስ ጋር የሚያሳልፉት ጊዜ በራሳቸው የሜዳ ክልል ብቻ ተገድቦ የታየው ዋልያዎቹ እስከ 19ኛው ደቂቃ ድረስ የጠራ የግብ ማግባት ሙከራ ማድረግ ተስኗቸው ነበር። በዚህም ደቂቃ ሙጂብ ቃሲም ከመስመር የተሻገረለትን ኳስ በግንባሩ ወደ ግብነት ለመቀየር ሞክሮ ወጥቶበታል። ጨዋታውን በሚፈልጉት መንገድ ሲቆጣጠሩ የነበሩት ዛምቢያዎች በ23ኛው ደቂቃ ሁለተኛ ጎል አስቆጥረው መሪነታቸውን አስፍተዋል። በዚህ ደቂቃ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ከኋላ ኳስ ለማስጀመር ባደረጉት ጥረት ሀብታሙ እና ታፈሰ ሲቀባበሉ ዛምቢያዎች ቀምተው የተሻማው ኳስ ሲመለስ ቻቡላ ወደ ግብ መቶ አቤል ሲመልሰው ያገኘውን ኳስ ሲኮምቤ በቀላሉ ወደ ግብነት ቀይሮታል። በዚህ ግብ ላይም እንደመጀመርያው ጎል ሁሉ የቅብብል ስህተት፣ ያልተደራጀ መከላከል እና የግብጠባቂ ድክመት በጉልህ ታይቷል።ፈጣን የመስመር ላይ ሽግግሮችን (ከመከላከል ወደ ማጥቃት) ሲከተሉ የነበሩት ቺፖሎፖሎዎቹ በተለይ በቀኝ መስመር በኩል የጥቃተቀቸውን ትኩረት በማድረግ ወደ ዋሊያዎቹ የግብ ክልል መድረስ ቀጥለዋል። በ36ኛው ደቂቃም በዛምቢያ የጎል ክልል ኮንድዋኒ ቺቦኒ ከኢትዮጵያ ተጫዋቾች ያስጣለው ኳስ በሁለት ቅብብል ብቻ ወደ ኢትዮጵያ የሜዳ ክፍል ደርሶ ኢማኑኤል ቻቡላ ረጅም ርቀት ኳሱን ይዞ በመግፋት ከሳጥኑ የቀኝ ክፍል መትቶ ለራሱ ሁለተኛ ለቡድኑ ሶስተኛ ጎል አስቆጥሯል። በዚህ ጎል ላይም ያልተናበበው የተከላካይ ክፍል ቻቡላ ከጨዋታ ውጪ አቋቋም ላይ እንዳይገኝ እና አምልጦ እንዲወጣ አድርጓል።ፈጣኑን የዛምቢያ ጥቃት መቋቋም የተሳናቸው ኢትዮጵያዎች ሦስተኛውን ግብ ካስተናገዱ ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ በተገኘ የቅጣት ምት ወደ ጨዋታው በቶሎ ለመመለስ ጥረዋል። ነገርግን ከርቀት የተገኘውን የቅጣት ምት ሱራፌል ወደ ጎልነት መቀየር ሳይችል ወጥቶበታል። የመጀመሪያው አጋማሽ ሊጠናቀቅ ደቂቃዎች ሲቀሩት አልበርት ካዋንዳ ዳግም ወደ ዋሊያው የግብ ክልል ደርሶ አራተኛ ጎል ለማስቆጠር ሞክሯል። በደቂቃ ልዩነትም አሚቲ ሻሜንዴ ያመቻቸለትን ነፃ ኳስ ከጎሉ ፊት ለፊት የነበረው ኮሊንስ ሲኮምቤ መትቶ የጎሉ አግዳሚ ለትሞ የወጣበት አጋጣሚ በመጀመርያው አጋማሽ የዛምቢያን መሪነት ወደ 4-0 ሊያሳድግ የሚችል ነበር።በሁለተኛው አጋማሽ አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ጌታነህ ከበደ፣ ጋዲሳ መብራቴ፣ ሀይደር ሸረፋ፣ ከነዓን ማርክነህ፣ አማኑኤል ዮሐንስ፣ መሳይ ፓውሎስ፣ አምሳሉ ጥላሁን፣ ሽመክት ጉግሳ እና ተክለማርያም ሻንቆን በሱሌማን፣ ኃ/ሚካኤል፣ አንተነህ፣ ሀብታሙ፣ ታፈሰ፣ ሙጂብ፣ ሱራፌል፣ አማኑኤል እና አቤል ተክቶ ወደ ሜዳ አስገብቷል። በዚህ አጋማሽም ዋሊያዎቹ በአንፃራዊነት የተሻለ የጨዋታ እንቅስቃሴ በማሳየት የግቡን ልዩነት ለማጥበብ ሲጥሩ ታይቷል። የአጋማሹን የመጀመሪያ ሙከራ ጋዲሳ በ52ኛው ደቂቃ ከቅጣት ምት ያደረገ ሲሆን ኳስ እና መረብ ግን ሳይገናኙ ቀርተዋል። ከሦስት ደቂቃዎች በኋላም ተቀይሮ የገባው ከነዓን ከአዲስ የተሻገረለትን ኳስ ከፍፁም ቅጣት ምት ሳጥን ጫፍ ላይ ሆኖ ወደ ጎል ቢመታትውም ኳስ ዒላማዋን ስታ ወታበታለች።ጨዋታውን በመጀመሪያው አጋማሽ ያገባደዱ የሚመስለው ዛምቢያዎች በዚህኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በርካታ ለውጦቸን በማድረግ አቅማቸውን ቆጥበው ተጫውተዋል። ፍጥነቶች የታከሉበት የመልሶ ማጥቃት እንቅስቃሴዎችንም ገድበው ታይተዋል። ይህ የተጋጣሚያቸው መቀዛቀዝ የጠቀማቸው ዋሊያዎቹ በበኩላቸው ባልተደራጀ መንገድ ቢሆንም በተለያዩ አማራጮች ወደ ግብ መድረሳቸውን ቀጥለዋል። በ60ኛው ደቂቃም ከርቀት የተገኘውን የቅጣት ምት ጌታነህ ከበደ ወደ ግብ መትቶት ግብ ጠባቂው ጃክሰን ካኩታ በቀላሉ አምክኖበታል። ይህንን ሙከራ ያደረገው ጌታነህ ከሦስት ደቂቃዎች በኋላም በቀኝ መስመር ያገኘውን ኳስ ዳግም ወደ ግብነት ለመቀየር ጥሮ ኳስ የግቡን የጎን መረብ ታካ ወጥታበታች።በመጀመሪያው አጋማሽ የጎንዮሽ እና የኋልዮሽ ኳሶችን አዘውትረው ሲጠቀሙ የነበሩት የአሠልጣኝ ውበቱ ተጫዋቾች በዚህኛው አጋማሽ በተረጋጋ መንፈስ የፊትዮሽ ኳሶችን በአንፃራዊነት በተሻለ መልኩ ለመጠቀም ሞክረዋል። በተለይም በሁለተኛው አጋማሽ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባውን ጌታነህ ከበደን ታሳቢ ያደረጉ ተንጠልጣይ እና ተከላካይ ሰንጣቂ ኳሶችን ቡድኑ ሲጠቀም ተስተውሏል። ከዚህ በተጨማሪም በ8 ቁጥር ቦታ የተሰለፉት ሀይደር እና ከነዓን ከሳጥን ውጪ በመሆን በተከላካዮች ተገጭተው የሚመለሱ ኳሶችን ወደ ግብነት ለመቀየር ጥረዋል። በዚህ አጨዋወትም ከነዓን በ80ኛው ደቂቃ ከቀኝ መስመር የተሻገረው ኳስ በተከላካዮች ተጨርፎ ሲመለስ ያገኘውን ኳስ ወደ ግብነት ለመቀየር ሞክሮ ነበር። ከሦስት ደቂቃዎች በኋላም በተመሳሳይ በተከላካዮች ተገጭቶ የተመለሰውን ኳስ በሳጥን ውስጥ የነበረው ጌታነህ በጥብቅ ምት ኳሷን ወደ ጎል ቢልካትም ዒላማዋን ስታ ወደ ውጪ ወጥታበታለች።በሁለተኛው አጋማሽ ድንቅ ብቃቱን ሲያሳይ የነበረው አምበሉ ጌታነህ ጨዋታው ሊገባደድ አምስት ደቂቃዎች ሲቀሩት ቡድኑን በባዶ ከመሸነፍ ያዳነች ኳስ ከመረብ አገናኝቷል። በዚህ ደቂቃ ሽመክት ጉግሳ በጥሩ ሁኔታ ወደፊት የጣለውን ኳስ ከነዓን ማርክነህ በአግባቡ ተቆጣጥሮ በጥሩ አቋቋም ላይ ለነበረው ጌታነህ አመቻችቶለት አምበሉ አጋጣሚውን ወደ ጎልነት ቀይሮታል። ዋሊያዎቹ በቀሩት ደቂቃዎች የግቡን ልዩነት ለማጥበብ ፍላጎት ቢያሳዩም ረጃጅሞቹም የዛምቢያ ተከላካዮች ማለፍ ተስኗቸዋል። ጨዋታውም በዛምቢያ ብሔራዊ ቡድን 3-1 አሸናፊነት ተገባዷል።", "passage_id": "ba9bb0a4642b831ed1797bbcd103746d" }, { "passage": "ከትናንት በስቲያ ለቻን 2020 የመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ጎረቤት ሃገር ጅቡቲን በደርሶ መልስ የገጠመው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአጠቃላይ 5-3 በሆነ ድምር ውጤት ለቀጣዩ ማጣሪያ አልፏል፡፡ ጅቡቲ ላይ ጎል ማግባት ተቸግሮ የነበረው ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ በአስቻለው ታመነ የፍጹም ቅጣት ምት ጎል 1-0 አሸንፎ በመልሱ ደግሞ ድሬ ዳዋ ላይ ደግሞ በጅቡቲ ተፈትኖ 4-3 በማሸነፍ ወደ ቀጣይ የማጣሪያ ዙር አልፏል፡፡ ከጨዋታው በኋላ የጅቡቲው አሰልጣኝ ጁሊያ ሜት ከሶከር ኢትዮጵያ ፈረንሳይኛ አዘጋጅ ጋር አጭር ቆይታ አድርገዋል።የድሬዳዋውን ጨዋታ እና ውጤቱን እንዴት አገኙት?ውጤቱን በተመለከተ ቢያንስ አቻ ይገባን ነበር። 3ለ3 ሆነን 88 ወይም 89ኛው ደቂቃ ላይ በገባብን ጎል ተሸንፈናል፤ በተለይ አቻ ከሆንን በኋላ 4-3 የምንሆንበትን ዕድል ማባከናችን የሚያስቆጭ ነው፡፡ በውጤቱ በጣም አዝኛለው። እንዳየኸው የኛ ልጆች ከጨዋታው በኋላ ሜዳ ላይ ሲያለቅሱ ነበር፡፡ በእግር ኳስ አይሆንም የሚባል ነገር አይኖርም፡፡ ጨዋታው በጣም ጥሩ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሜዳ 3 ማግባት ቀላል አይደለም፤ ይህንን በቅርብ ጊዜ ማድረግ የቻለው የአልጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ብቻ ነበር፣ ይህን አሳክተናል፡፡ ከመጀመሪያው ጨዋታ በኋላ አምበላችንን ጨምሮ የተጎዱብን ተጫዋቾች ነበሩ፡፡ በተለይ መከላከሉ ላይ በጣም ጥሩ ነበርን፡፡ የኢትዮጵያ ቡድን ምንም ነገር መፍጠር እንዳይችል አስበን ገብተን ተሳክቶልናል፡፡ የሁለቱንም ቡድኖች ከተመለከትክ የተጋጠምነው ከፍተኛ ልምድ ካላቸው ልጆች ጋር ነው፡፡ የተጫዋቾቹን ተክለ-ቁመና ካየህ ደግሞ የኛ ልጆች በጣም ደቃቃ ናቸው፡፡ ጨዋታው ላይ ግን የበለጠ የጨዋታ ብቃትና የማሸነፍ ፍላጎት የነበረው ግን የኛ ልጆች ጋር ነው፡፡ በተጫዋቾቼ በጣም ኮርቻለው፡፡በአፍሪካ በቆዳ ስፋታቸው ትልቅ ከሚባሉ ሃገራት አንዷ የ100 ሚሊዮን ህዝብ እናት ኢትዮጵያ በአግባቡ አንድ ሚሊዮን እንኳን የማይሞላ ህዝብ ካላት ከጅቡቲ ጋር የዳዊትና ጎሊያድን ያህል ልዩነት አላቸው፡፡ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ኬንያና ጋናን የመሳሰሉ ቡድኖች በምድቧ ስለነበሩ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ባትችልም የተደራጀና በአግባብ የተያዘ ብሔራዊ ቡድን አላት፡፡ ጅቡቲ ላለፉት ሁለት ዓመታት ብሔራዊ ቡድን እንኳ አልነበራትም፡፡ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ከወሰድክ ኢትዮጵያውያን የዓለም አቀፍ ውድድር ልምድ አላችሁ። የኛ ልጆች ተሰብሰበው መዘጋጀት ከጀመሩ ሁለት ወር አልሞላቸውም፡፡ ይህ ውጤት ለኛ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡ በተለይ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በአካል ብቃት ልቀን መገኘት ለኛ ቀላል አይደለም፡፡ ከእረፍት መልስ እኛ ሙሉ ለሙሉ በልጠን ነበር፤ ኢትዮጵያውያን ከኛ በባሰ ሁኔታ ደክመው ነበር የቀረቡት፡፡ የግብ ዕድልም በመፍጠር ቢሆን እኛ የተሻልን ነበርን፡፡ ጨዋታውንና ውጤቱን ስታይ ለኛ ውጤቱ አስደሳች ሊሆን አይችልም፡፡ ከዚህ በፊት ኢትዮጵያ ጅቡቲን ስትገጥም አምስት ለምንም፣ አራት ለምንም ነበር የምታሸንፈው። አሁን ግን ይሄ ቡድን እንደዚያ አይደለም፡፡ይህን ብሔራዊ ቡድን የተረከቡት መቼ ነው?ጥር ወር መጨረሻ ላይ ነው ወደ ጅቡቲ የመጣሁት። የመጀመሪያዎቹን ሦስት ወራት የሃገሪቱን ሻምፒዮና ሳስተውል ነበር፤ ተጫዋቾቹን ሰብስቤ ዝግጅት ከጀመርኩ ግን ገና ሁለት ወሬ ነው፡፡ ሃያ ዘጠኝ ተጫዋቾች ከሃገሪቱ ሊግ ይዤ ነው ዝግጅት የጀመርኩት፡፡ ይሄ ቡድን የሁለት ወራት ዝግጅት ውጤት ነው፡፡ ወደፊት ጥሩ ነገር ይታየኛል፡፡ቡድኑን ከተረከቡ በኋላ ምን ተስፋ ምን ስጋት ተመለከቱ ?የመጀመሪያዎቹን ሁለት ጎሎች ያስቆጠሩት ተጫዋቾች የ19 እና የ20 ዓመት ታዳጊዎች ናቸው፡፡ ለብሔራዊ ቡድንም ለመጀመሪያ ጊዜ መጠራታቸው ነው፡፡ ጅቡቲ ላይ ስንጫወት ከተሰለፉት 11 ተጫዋቾች ከግማሽ በላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ለብሔራዊ ቡድን የተጠሩ ዕድሜያቸው ከሃያ ዓመት በታች የሆነ ታዳጊዎች ናቸው፡፡ ይህ ቡድን ከዚህ በላይ የማደግ ተስፋ ያለው ብሔራዊ ቡድን ነው፡፡ከጨዋታው በኋላ ስሜትዎ ምን ነበር ?ክብር.. ኩራት… ቅድም እንደነገርኩህ የቡድናችን አምበል በጉዳት የመልሱን ጨዋታ አላደረገም፡፡ ሌላ የቡድናችን ወሳኝ የመሃል ሜዳ ተጫዋች እሱም በጉዳት የመልሱን ጨዋታ አልተጫወተም፡፡ ዛሬ ቡድናችንን ሲመራ የነበረው አዲሱ አምበል የመጀመሪያዎቹን ሃያና ሃያ አምስት ደቂቃዎች የተቸገረ ይመስል ነበር፣ ነገር ግን እንደገና ወደጨዋታ ተመልሶ ያሳየን ነገር እጅግ የሚያኮራ ነው፡፡ በርግጥ ተጫዋቾቼ ከጨዋታው በኋላ ሜዳ ላይ ሲያለቅሱ ሳይ ሃዘን ተሰምቶኛል፡፡ ማሸነፍ ይገባን ነበር፡፡ ከጨዋታው አንድ ቀን በፊት ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሁለት ለዜሮ እናሸንፋለን ብዬ ነበር፣ ጨዋታውን ሳይ ደግሞ በጣም ነው የተቆጨሁት፤ ማሸነፍ ነበረብን፡፡እኔም ዜናውን አይቼዋለው በጣም ገርሞኝ ነበር ሁለት ለዜሮ እናሸንፋለን ነው ወይስ ከሁለት በላይ አይገባብንም ነው ያሉት?ሁለት ለዜሮ እናሸንፋለን ነው ያልኩት። አይገባብንም ተብሎ ከተሰራ በጣም ነው የሚገርመኝ። እኔ ሁለት ለባዶ እናሸንፋለን ነው ያልኩት። ምክንያቱም ለማለፍ ሁለት ማግባት ይጠበቅብናል።ከጨዋታው በኋላ ይህን ወይም ያን ብናረግ የሚል ምናልባት የጸጸት ስሜት?በፍጹም! በነገራችን ላይ ብዙ ነገር ነው አሸንፈን የወጣነው። 3 ጎል ከሜዳችን ውጭ አግብተናል። ያውም ኢትዮጵያ ላይ ጨዋታ ተቆጣጥረን ሙሉ ለሙሉ በሚያስብል የጨዋታ ብልጫ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የበለጠ የግብ ዕድል መፍጠር ችለናል። ስለዚህ እኔ ተሸንፈናል ብዬ አላስብም፡፡ያለደጋፊ መጫወታችሁ ለእንግዳ ቡድን አድቫንቴጅ ነው፤ ያንን አለመጠቀማችሁስ ?ድሬዳዋና ጅቡቲ ካላቸው ቅርበት የተነሳ የድሬዳዋ ነዋሪ የጅቡቲን ተጫዋቾች ከኢትዮጵያ ተጫዋቾች በላይ ያውቃቸዋል፡፡ ከጅቡቲ የመጡ በርካታ ደጋፊዎች ነበሩን፤ በርካታ ጅቡቲያውያን ድሬዳዋ ይገኛሉ አሁን ደግሞ በተለይ ወቅቱም ክረምት ስለሆነ በሙቀት ምክንያት ድሬዳዋ የሚኖር በርካታ የጅቡቲ ሰው አለ፡፡ ያለህዝብ መጫወታችን ለኛ ከጥቅሙ ጉዳቱ ነው የሚያመዝነው፡፡ በደጋፊ ፊት ብንጫወት ምናልባት ውጤቱ ሊቀየር ይችል ነበር፡፡ከጨዋታው በኋላ ለተጫዋቾችዎ ምን አሏቸው ?አመሰግናለው ነዋ! ምን እላቸዋለው፡፡ ኢትዮጵያውያንን ገጥማችሁ በሜዳቸው ሦስት ጎል አግብታችኋል፡፡ ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያውያን አራትና አምስት አያገቡባችሁም፤ ታሪክ ቀይራችኋል፤ እንኳን ደስ ያላችሁ ነው የምላቸው፡፡ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የሚሉት ካለ?እንኳን ደስ ያላችሁ። በመጀመሪያው ጨዋታ በሃገራችን መጥታችሁ በማሸነፋችሁ አልፋችኋል። የጨዋታው ህግ በነጥብና በጎል የበለጠ ያልፋል ነው። ስለዚህ እንኳን ደስ ያላችሁ፤ ከዚህም በኋላ መልካም ዕድል።", "passage_id": "247454f643a70c7c0f760f4eb2ff9282" }, { "passage": "በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በእግር ኳስ ለመሳተፍ የአፍሪካ አገራት ሁለተኛውን የደርሶ መልስ የማጣሪያ ጨዋታዎችን ካለፈው ሳምንት ጀምሮ አከናውነዋል። በዋናው ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ አብርሃም መብራቱ እየተመራ ከሁለት ሳምንት ላላነሰ ጊዜ ሲዘጋጅ የቆየው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ኦሊምፒክ ቡድን ማጣሪያውን ሳያልፍ ቀርቷል። ባለፈው ሐሙስ የመጀመሪያውን ጨዋታ በሜዳው ከማሊ አቻው ጋር ያደረገው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ኦሊምፒክ ቡድን አንድ ለአንድ መለያየቱን ተከትሎ ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋው አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ ነበር። እንደ ተሰጋውም ከትናንት በስቲያ ምሽት ወደ ባማኮ አቅንቶ ከሜዳው ውጪ ያደረገውን የመልስ ጨዋታ አራት ለዜሮ ተሸንፏል።በዚህም መሠረት 5ለ1 በሆነ ድምር ውጤት ወደ ቀጣዩ ዙር ሳያልፍ ቀርቷል። እአአ 2004 ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦሊምፒክ እግር ኳስ የተሳተፈችው ማሊ ወደ መጨረሻውና ሦስተኛው ዙር ማጣሪያ ስታልፍ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የመሳተፍ ዕድሏ በጊዜ ከስሟል። ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የማጣሪያ ጨዋታ ሶማሊያን በሜዳዋና በገለልተኛ ሜዳ በሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏ ይታወሳል። ማሊን ጨምሮ አስራ ስድስት የአፍሪካ አገራት ቀጣዩን ዙር መቀላቀላቸውን ካለፈው ሰኞ ጀምሮ አረጋግጠዋል። ያለፈው የአፍሪካ ከሃያ ሦስት ዓመት በታች ዋንጫ አሸናፊዋ ናይጀሪያ ቀጣዩን ዙር ከተቀላቀሉ አገራት መካከል ስትገኝ ሞሮኮ ባልተጠበቀ መልኩ በጊዜ ተሰናባች ሆናለች። ሁለተኛው የማጣሪያ ጨዋታ መጠናቀቁን ተከትሎ ያለፉት አገራት በሦስተኛው ዙር የሚገጥሙትን አገር ማወቅችለዋል። በመጨረሻውና ሦስተኛው ዙር የማጣ ሪያ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ ዚምባቡዌን ስትገጥም ዛምቢያ ከኮንጎ ብራዛቪል፣ጋና ከአልጄሪያ፣ካሜሩን ከቱኒዚያ፣ኮትዲቭዋር ከጊኒ፣ ሱዳን ከናይጄሪያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከማሊ የሚገናኙ ይሆናል። የዓለማችን ትልቁ የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ በሩቅ ምሥራቋ አገር ጃፓን ቶኪዮ ከተማ ሊካሄድ ከሁለት ዓመት ያነሰ ጊዜ ይቀረዋል። በዚህ ኦሊምፒክ ላይ ለመሳተፍ እንደ እግር ኳስ ያሉ የስፖርት ዓይነቶች ረጅም የማጣሪያ ጨዋታዎችን ስለሚሹ ከወዲሁ እየተከናወኑ ይገኛል። በአፍሪካ ዞን ሦስተኛውን የማጣሪያ ጨዋታ የሚያሸንፉ ስምንት አገራት የሚለዩ ቢሆንም በቀጥታ ወደ ኦሊምፒክ አያመሩም። እነዚህ ስምንት አገራት ከዓመት በኋላ ግብፅ ለምታዘጋጀው ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ በቀጥታ የሚያልፍ ይሆናል። በዚህ አፍሪካ ዋንጫ ላይ መሳተፍ ብቻ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚያበቃም አይደለም። በአፍሪካ ዋንጫው ከአንድ እስከ ሦስት ያለውን ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ አገራት በኦሊምፒኩ ተሳታፊ መሆናቸውን ያረጋግጣሉ። የወንዶቹ የኦሊምፒክ ጉዞ እዚህ ላይ ያበቃ ቢሆንም በአሰልጣኝ ሠላም ዘራይ የሚመራው የኢትዮጵያ ሴቶች ኦሊምፒክ ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ምዕራፍ ዝግ ጅቱን በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል። አሰልጣኝ ሠላም ዘራይ በሁለተኛ ምዕራፍ ዝግጅቷ የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ከመሰል ሀገራት ጋር ለማድረግ ያደረገችው ጥረት የተሳካ አይመስልም። ያም ሆኖ የሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ መጋቢት 25 የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታቸውን በአዲስ አበባ ስቴዲየም የሚያደርጉት የኦሊምፒክ ሴቶች ቡድን የመልስ ጨዋታቸውን ከሦስት ቀን በኋላ በዩጋንዳ ካምፓላ የሚያደርጉ ይሆናል። እንስቶቹ በደርሶ መልስ ጨዋታ ድል የሚቀናቸው ከሆነም ቀጣይ ተጋጣሚያቸው ካሜሩን እንደምትሆን ካፍ አሳውቋል። ይህ ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ በግብፅ ሲካሄድ ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን ውድድሩን ለማዘጋጀት ታጭታ የነበረችው ዛምቢያ ነበረች። ይሁን እንጂ ካፍ ይህን ዕድል 2017 መስከረም ወር ላይ ለግብፅ መስጠቱ ይታወሳል። ናይጄሪያ ያለፈው ውድድር ቻምፒዮን መሆኗም አይዘነጋም። በኦሊምፒክ መድረክ በእግር ኳስ የሚሳተፉ ተጫዋቾች ዕድሜያቸው ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የሆኑ ብቻ ቢሆንም አንድ አገር ዕድሜያቸው ከሃያ ሦስት ዓመት በላይ የሆኑ ሦስት ተጫዋቾችን የማሰለፍ ዕድል ይኖረዋል። በሴቶች በኩል ግን በኦሊምፒክ እግር ኳስ ለመሳተፍ የዕድሜ ገደብ አልተቀመጠም። ጃፓን በኦሊምፒኩ የእግር ኳስ ጨዋ ታዎችን ለማስተናገድ በመዲናዋ ቶኪዮ ብቻ ሳትወሰን ሌሎች ከተሞችንም የውድድሩ መዳረሻ ማድረጓ ይታወሳል። ከቶኪዮ በተጨማሪ ኢባራኪ፤ ሴታማ፤ ሳፓሮ፤ ሴንዳይና ዮኮሃማ የእግር ኳስ ውድድሮችን የሚያስተናግዱ ከተሞች ናቸው። ብራዚል ባስተናገደችው የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ በወጣት ቡድኗ አማካኝነት በወንዶች ቻም ፒዮን መሆኗ የሚታወስ ሲሆን ጀርመን በሴቶች ቻምፒዮን መሆን ችላለች።አዲስ ዘመን መጋቢት 19/2011በቦጋለ አበበ", "passage_id": "d6a217a2b323396b881854d75aa583f6" }, { "passage": "የ21ኛው ሳምንት ማሳረጊያ እንደሚሆን የሚጠበቀው የጦሩ እና የዐፄዎቹን ጨዋታ እንደሚከተለው ዳሰነዋል።\nነገ አዲስ አበባ ላይ ዘግየት ብሎ በ10፡00 የሚጀምረው ጨዋታ በርካታ ግቦች በማስተናገድ ከፊት የተቀመጠው መከላከያ እምብዛም መረባቸውን ከማያስደፍሩ ክለቦች መካከል አንዱ የሆነው ፋሲል ከነማን ያስተናግዳል። የድል ብርሀንን ካዩ ሰባት ሳምንታት ያለፏቸው መከላከያዎች ዳር ዳር ሲሉ ወደነበሩበት ወራጅ ቀጠና ገብተው እንዲሁም ከአሰልጣኝ ስዩም ከበደ ጋር ተለያይተው ነው ፋሲልን የሚገጥሙት። መከላከያዎች የሚቆጠሩባቸውን ግቦች መቀነስ ቢችሉም በመጨረሻዎቹ ሁለት ጨዋታዎች በአንድ ጎል ልዩነት ለሽንፈት መዳረጋቸው አልቀረም። ካለፉት ሁለት ጨዋታዎች ሁለት ነጥቦችን ብቻ ያሳኩት ፋሲሎችም በሜዳ ላይ እንቅስቃሴ መልካም ነገር ቢታይባቸውም መሪውን በነጥብ ቀርበው ማስጨነቅ የሚችሉባቸውን አጋጣሚዎች አምክነዋል። በሲዳማ የተነጠቁትን የሁለተኛነት ደረጃ ዳግም ለመረከብም ከመዲናዋ በድል መመለስ ይጠበቅባቸዋል።በአሰልጣኝ በለጠ ገብረኪዳንን መሪነት የመጀመሪያ ጨዋታቸውን የሚያደርጉት መከላከያዎች ምን ዓይነት ለውጦችን አድርገው እንደሚመጡ ለመናገር ይከብዳል። ሆኖም በአሰልጣኝ ለውጦች ማግስት ቡድኖች የሚያሳዩት የመንፈስ ንቃት በጦሩም በኩል የሚጠበቅ ነው። ከዚህ ውጪ አሰልጣኙ ከዚህ ቀደም ቡድኑን በያዙበት ወቅት ቀጥተኛነትን በተላበሰ መልኩ በቶሎ ወደ ጎል የሚደርስ ቡድን ይዘው እንደሚቀርቡ ሲገመት የተከላካይ ክፍሉን ተደጋጋሚ ስህተቶች እና በቀላሉ በተጋጣሚ የአማካይ ክፍል እየተዋጠ የመጨረሻ ኳሶችን ማድረስ የሚቸግረውን የመሀል ክፍሉን በቶሎ የማከም አጣዳፊ ኃላፊነት ይኖርባቸዋል። መከላከያ የፊት አጥቂው ምንይሉ ወንድሙን በጉዳት ተከላካዩ አበበ ጥላሁንን ደግሞ በቅጣት በነገው ጨዋታ መጠቀም አይችልም።የአሰልጣኝ ውበቱ አባተው ፋሲል ከነማ አንድ የተከላካይ መስመር ተጨዋችን መስዋት በማድረግ ከኋላ በሦስት በሚጀምር አሰላለፍ የሚቀርብበትን አኳኋን በመቀየር የተወሰኑ የተጫዋች ለውጦችን በማድረግ ወደ ሜዳ እንደሚገባ ይጠበቃል። በአጫጭር ቅብብሎች የኳስ ቁጥጥር የበላይነትን በመያዝ ለማጥቃት የሚሞክረው የቡድኑ የአማካይ ክፍል በተረጋጋ መንገድ ጫና መፍጠር መቻል ከነገ ተጋጣሚው ደካማ ጎን አንፃር ተጠቃሚ ሊያደርገው የሚችል ሲሆን የአጥቂው ሙጂብ ቃሲም ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ግብ ማስቆጠሩ መመለሱ ለጦሩ የኋላ ክፍል ተጨማሪ ስጋት መሆኑም አይቀርም። ለፋሲሎች በጨዋታው መጥፎው ዜና በሚመርጡት አጨዋወት ከኋላ ቅብብሎችን ለመጀመር ተመራጭ የሆነው ተከላከያቸው ያሬድ ባየህ ጉዳት ሲሆን የሱራፌል ዳኛቸው መሰለፍም አጠራጣሪ ሆኗል።የእርስ በርስ ግንኙነት እና እውነታዎች– ሁለቱ ክለቦች በሊጉ ለ6 ጊዜያት ተገናኝተው ዕኩል ሁለት ሁለት ጊዜ በመሸናነፍ ሁለት ጊዜ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል፡፡ በጨዋታዎቹ ፋሲል ስምንት ግቦችን ሲያስቆጥር መከላከያ ስድስት ጊዜ ኳስ እና መረብን አገናኝቷል፡፡– አዲስ አበባ ላይ ዘጠኝ ጊዜ የክልል ቡድኖችን የገጠመው መከላከያ አንድ ጊዜ ብቻ ድል ሲቀናው ሦስቴ ነጥብ ተጋርቶ በአምስት ጨዋታዎች ተሸንፏል።– ፋሲሎች ከጎንደር ወጥተው ባደረጓቸው አስር ጨዋታዎች ስድስት ጊዜ ነጥብ ሲጋሩ ሁለት ጊዜ ድል አድርገው በሌሎች ሁለት ጨዋታዎች ደግሞ ተሸንፈዋል።ዳኛ– መከላከያን ከጊዮርጊስ እንዲሁም ፋሲል ከነማን ከሀዋሳ ያጫወተው ኢንተርናሽናል ዳኛ ዳዊት አሳምነው ይህን ጨዋታ ይመራዋል። አርቢትሩ እስካሁን በዳኘባቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች አንድ የፍፁም ቅጣት ምት እና አንድ የቀጥታ ቀይ ካርድ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ 29 የማስጠንቀቂያ ካርዶችንም መዟል።ግምታዊ አሰላለፍመከላከያ (4-4-2)አቤል ማሞሽመልስ ተገኝ – ምንተስኖት ከበደ – አዲሱ ተስፋዬ – ዓለምነህ ግርማሳሙኤል ታዬ – ቴዎድሮስ ታፈሰ – ዳዊት እስጢፋኖስ – ፍሬው ሰለሞንተመስገን ገብረኪዳን – ፍፁም ገብረማርያምፋሲል ከነማ (4-3-3)ሚኬል ሳማኬሰዒድ ሁሴን – ከድር ኩሊባሊ – ዓይናለም ኃይለ – አምሳሉ ጥላሁንኤፍሬን ዓለሙ – ሀብታሙ ተከስተ – ሱራፌል ዳኛቸውኢዙ አዙካ – ሙጂብ ቃሲም – ሽመክት ጉግሳ", "passage_id": "c228783fdf498882357fcebd66638f53" } ]
84a739e96d82e1c15aad0069d9a30dcf
9a8011dfb402f8a8d44870896ce6e824
ለተሰንበት ግደይ የዓለም ክብረወሰን አሻሻለች
ኢትዮጵያዊቷ ወጣት አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አስራ አምስት ኪሎ ሜትር ክብረወሰንን መጨበጥ ችላለች፡፡ ለተሰንበት ከትናንት በስቲያ በኔዘርላንድስ ‹ሰቨን ሂልስ ረን› በተባለ የጎዳና ላይ ውድድር ክብረወሰኑን ያሻሻለች ሲሆን ውድድሩን ያጠናቀቀችበት ሰዓት 44፡20 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ከወር በፊት በዶሃው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በአስር ሺ ሜትር አስደናቂ ብቃት በማሳየት የብር ሜዳሊያ ማሸነፍ የቻለችው ለተሰንበት በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና በወጣቶች ምድብ ለሁለት ተከታታይ ዓመታት ቻምፒዮን እንደነበረች ይታወሳል፡፡ ለተሰንበት የዓለም የአስራ አምስት ኪሎ ሜትር ክብረወሰንን ከአንድ ደቂቃ በላይ ያሻሻለች ሲሆን ይህ ክብረወሰን ከሁለት ዓመት በፊት በኬንያዊቷ ጆይስሊን ጂፕኮስጌ 45፡37 በሆነ ሰዓት በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የተመዘገበ መሆኑን የዓለም አትሌቲክስ ድረ ገፅ ዘገባ አመልክቷል፡፡ የሃያ አንድ ዓመቷ አትሌት ለተሰንበት ከውድድሩ በኋላ ‹‹ገና ለውድድሩ ዝግጅት ሳደርግ በጥሩ አቋም ላይ እንዳለሁ አውቅ ነበር፣ በውድድሩም ላይ ምቾት ተሰምቶኛል፣ እውነቱን ለመናገር የቀድሞውን ክብረወሰን በምን ያህል ሰዓት እንዳሻሻልኩኝ ለማየት ጓጉቼ ነበር›› በማለት የዓለም ክብረወሰን ስለመጨበጧ እርግጠኛ እንደነበረች ተናግራለች፡፡ ለተሰንበት ውድድሩን ከማሸነፏና የዓለም ክብረወሰን ከማሻሻሏ ባሻገር የመጨረሻዎቹን አስር ኪሎ ሜትሮች የሮጠችበት ፍጥነት የአትሌቲክሱን ቤተሰብ ያስደነቀና ወደ ፊት ትልቅ ተስፋ እንዲጣልባት ያደረገ ነበር፡፡ ለተሰንበት የመጨረሻዎቹን አስር ኪሎ ሜትሮች 29፡12 በሆነ ሰዓት ያገባደደች ሲሆን ይህም አልማዝ አያና በ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ የአስር ሺ ሜርት የዓለም ክብረወሰንን ስታሻሽል ካስመዘገበችው 29፡17፡45 ሰዓት የፈጠነ ነው፡፡ የአስራ አምስት ኪሎ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ 2009 ላይ በተመሳሳይ ውድድር በጥሩነሽ ዲባባ ተሻሽሎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ጥሩነሽ በወቅቱ የርቀቱን ክብረወሰን 46፡28 በሆነ ሰዓት ስታሻሽል ከእሷ በፊት ክብረወሰኑ 46፡55 በሆነ ሰዓት በጃፓናዊቷ ካዮኮ ፉኩሺ የተያዘ ነበር፡፡ ጥሩነሽ ይህን ክብረወሰን ባስመዘገበችበት ውድድር በወንዶች ባለቤቷ አትሌት ስለሺ ስህን ከዩጋንዳዊው ኒኮላስ ኪፕሮኖ ጋር እስከ መጨረሻ አንገት ለአንገት ተናንቆ በተመሳሳይ ሰዓት በመግባት አሸናፊ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ለተሰንበት በነገሠችበት የዘንድሮው ዓመት ውድድር በስቶች ኬንያዊቷ ኢቫሊን ቺርቺር 46፡32 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ሌላኛዋ ኬንያዊት ኢቫ ቺሮኖ 48፡14 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ፈፅማለች፡፡ በወንዶች መካከል የተካሄደውን ውድድር የሃያ ሦስት ዓመቱ ዩጋንዳዊ ስቲፈን ኪሳ 41፡49 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችሏል፡፡ እሱን ተከትለው ኬንያውያኑ ኤድዊን ኪፕቶ በሁለት ሰከንድ ዘግይቶ ሁለተኛ፣ ሞሰስ ኮይች በ42፡05 ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል፡፡አትሌት ለተሰንበት ግደይ ክብረወሰን ከማሻሻል ባለፈ ያሳየችው አስደናቂ አቋም ተስፋ እንዲጣልባት አድርጓል፣አዲስ ዘመን ህዳር 9 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22774
[ { "passage": " እየተጋመሰ የሚገኘው የሚያዝያ ወር በዓለም ላይ በርካታ የጎዳናና የማራቶን ውድድሮች የሚስተናገዱበት ነው። ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ በሰጣቸው የተለያዩ ውድድሮች ከፍተኛ ድል በማስመዝገብ ገፍተውበታል። ባሳለፍነው ሳምንት እንኳን ፓሪስና ቦስተን ማራቶኖች ላይ አስደናቂ ድሎችን በማስመዝገብ የረጅም ርቀት ኮከብነታቸውን ለዓለም ማሳየት ችለዋል። ዛሬና ነገ በሚካሄዱ የማራቶንና የግማሽ ማራቶን ዓለም አቀፍ ውድድሮችም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከወዲሁ ለድል ታጭተዋል። የወርቅ ደረጃ የተሰጠው ዶንግዪንግ ዓለም አቀፍ ማራቶን ዛሬ ሲካሄድ በሁለቱም ፆታ የቦታው ክብረወሰን ይሻሻላል ተብሎ ይጠበቃል። በውድድሩ በተለይም በሴቶች ከዚህ ቀደም አሸናፊ የነበረችው ዋጋነሽ መካሻ ዳግም ለአሸናፊነት መታጨቷን አዘጋጆቹን ጠቅሶ አይ.ኤኤ.ኤፍ በድረ ገፁ አስነብቧል።ባለፈው ጥር ወር በዱባይ ማራቶን አራተኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ 2:22:45 የሆነ የግል ምርጥ ሰዓቷን በማራቶን ያስመዘገበችው ዋጋነሽ በርቀቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተስፋ ከሚጣልባቸው ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አንዷ ነች። የመጀመሪያ የማራቶን ውድድሯን እአአ 2014 ሲንጋፖር ላይ ካደረገች ወዲህ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየች የምትገኘው የ27 ዓመቷ አትሌት፣ ባለፈው ዓመት በቻይና ሄንግሹ ያሸነፈችበትን ውድድር ጨምሮ በአራት ውድድሮች የተሻለ ሰዓት እያስመዘገበች መምጣቷ በዛሬው ውድድር ከአሸናፊነት ባለፈ ክብረወሰን ለማሻሻል አቅም እንዳላት እምነት ተጥሎባታል። ባለፈው ዓመት በለተብርሃን ሃይላይ የተመዘገበው 2:24:45የውድድሩ ክብረወሰን ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ከኬንያውያን ተፎካካሪዎቿ ጋር ልታሻሽለው ትችላለች ተብሎ ይጠበቃል።ለዚህም በውድድሩ የመጀመሪያውን ፈጣን ሰዓት የያዘችው ኬንያዊት ካሮሊን ቼፕታኑይ ያላት ጥንካሬ ፈጣን ሰዓት ሊመዘገብ እንደሚችል ማሳያ ተደርጓል። ይህች አትሌት 2:22:34 የሆነ ግል ፈጣን ሰዓት በርቀቱ ማስመዝገብ የቻለች ሲሆን፣ እአአ 2013 በፍራንክፈርት ማራቶን ባሸነፈችበት ውድድር ነበር ሰዓቱን ያስመዘገበችው። የ38 ዓመቷ ኬንያዊት እአአ 2016 የዴጉ ማራቶንን 2:27:39 በሆነ ሰዓት ካሸነፈች ወዲህ ባደረገቻቸው ውድድሮች ርቀቱን ከ2፡30 በታች ማጠናቀቅ አልቻለችም። ባለፈው ዓመትም በዚሁ ዶንግዪንግ ማራቶን አምስተኛ ሆና ስትፈፅም ማስመዝገብ የቻለችው ሰዓት 2፡34፡39 ነው።ይህም የአሸናፊነቱ ግምት ወደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት እንዲያደላ አድርጓል። ከዚህ ውድድር ክብረወሰን የተሻለ የራሷ ፈጣን ሰዓት ያላት ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አፈራ ጎደፋይ ለአሸናፊነት ከታጩ አትሌቶች መካከል ተካታለች። የ27 ዓመቷ አትሌት ባለፈው ዓመት በሻንጋይ ማራቶን አራተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ቀድሞ በርቀቱ የነበራትን ፈጣን ሰዓት ከአምስት ደቂቃ ባላነሰ በማሻሻል\n2:23:54 ማስመዝገቧ ይታወሳል። በዚሁ ውድድር በወንዶች መካከል የሚኖረው ፉክክር በኢትዮጵያዊው ግርማይ ብርሃኑ አሸናፊነት እንደሚደመደም ይጠበቃል። እአአ 2014 ዱባይ ማራቶን ላይ ሦስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡05፡49 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያስመዘገበው የ32 ዓመቱ ግርማይ የዴጉ ማራቶንን ባሸነፈበት ውድድር ተቀራራቢ የሆነ 2፡07፡26 ሰዓት አስመዝግቧል። የቀድሞው የራባት ማራቶን ሻምፒዮን ፍቃዱ ከበደም ባለፈው የዱባይ ማራቶን የራሱን ምርጥ ሰዓት በሰባ ሰከንድ አሻሽሎ\n2:08:27 ማጠናቀቁን ተከትሎ ለአሸናፊነት ይጠበቃል።በዚሁ በቻይና የወርቅ ደረጃ ተሰጥቶት ነገ በሚካሄደው ያንግዞ ዓለም አቀፍ ማራቶን የቀድሞ የውድድሩ ሻምፒዮን የሆነች ኢትዮጵያዊቷ ሱቱሜ አሰፋ የአሸናፊነት ግምት አግኝታለች።\n2017 ላይ የዚህ ውድድር አሸናፊ የነበረችው የ24 ዓመቷ ሱቱሜ ከሁለት ዓመት በፊት ለድል ስትበቃ 1፡10፡30 በሆነ ሰዓት አጠናቃለች። ባለፈው የሚላን ግማሽ ማራቶን ውድድር የራሷን ምርጥ ሰዓት ወደ 1፡07፡54 ማሻሻሏ ይታወሳል። በዚህ ውድድር ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ደጊቱ አዝመራው ቀላል ግምት የሚሰጣት አትሌት አይደለችም። የ20 ዓመቷ ደጊቱ በዚህ ዓመት ገና በመጀመሪያዋ የግማሽ ማራቶን ውድድር\n1:06:47 ሰዓት በማስመዝገብ ጥንካሬዋን ማሳየት ችላለች። ከሁለት ወራት በፊትም በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የራክ ግማሽ ማራቶን ውድድር አራተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ሰዓቷን ወደ1:06:07 አሻሽላለች። የዚህ ውድድር የአራት ጊዜ አሸናፊው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሞስነት ገረመው በሌለበት የዘንድሮው ውድድር ትውልደ ኬንያዊው የባህሬን አትሌት አብረሃም ቺሮበን የአሸናፊነት ግምት ወስዷል። ቺሮበን በነገው ውድድር እአአ 2015 በሞስነት ገረመው 59፡52 ሰዓት ተይዞ የቆየውን የቦታውን ክብረወሰን ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል። ቺሮበን ባለፈው ዓመት በውድድሩ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁም አይዘነጋም።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 12/2011 ", "passage_id": "5c796f4cfdda948382c981eb2d1363d0" }, { "passage": "ያለፈው ሳምንት በአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ ታላላቅ ውድድሮች የተስተናገዱበት ሆኖ አልፏል። ከቤት ውስጥ በርካታ ውድድሮች አንስቶ እስከተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮችም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በድል ተንቆጥቁጠው ታይተዋል። ከጣፋጭ ድሎቻቸው ባሻገርም በተለያዩ ርቀቶች ፈጣን ሰዓቶችና ክብረወሰኖች ማስመዝገብ ችለዋል። ትናንት ማለዳ በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ በተካሄደው የራስ አል ኪማህ ግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን ያስመዘገቡት ውጤት በጉልህ የሚጠቀስ ሲሆን በሁለቱም ፆታ ፈጣን ሰዓቶች ተመዝግቦበታል። በሴቶች መካከል በተካሄደው ውድድር ሰንበሬ ተፈሪ በርቀቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳትፋ 1፡05፡45 በሆነ ሰዓት አሸናፊ ሆናለች። ይህም በታሪክ በርቀቱ የመጀመሪያ ተሳትፎ የተመዘገበ ፈጣን ሰዓት ሲሆን የኢትዮጵያ ክብረወሰን ሆኖ ሊመዘገብም ችሏል። እጅግ ጠንካራ ፉክክር በታየበት ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ አራት ባለው ደረጃ ውስጥ ሲያጠናቅቁ የዓለም ግማሽ ማራቶን የክብረወሰን ባለቤት የሆነችው ነፃነት ጉደታ እስከ መጨረሻ ድረስ ታግላ ለጥቂት በመቀደሟ በተመሳሳይ ሰዓት ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ዘይነባ ይመር 1:05:46 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ሆና ስትፈፅም ደጊቱ አዝመራው በ1:06:07 ሰዓት ተከታዩን ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በዚህ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች እስከ መጨረሻ ያደረጉት አጓጊ ፉክክር ከአንድ እስከ ሦስት ባለው ደረጃ ያጠናቀቁ አትሌቶች የገቡበት ሰዓት ልዩነት የአንድ ሰከንድ ብቻ እንዲሆን አድርጎታል። በተመሳሳይ በወንዶች መካከል በተካሄደው ውድድር ለድል ሲጠበቁ የነበሩ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ቀዳሚውን ደረጃ በኬንያዊው ስቲፈን ኪፕሮፕ ቢነጠቁም ሁለተኛና ሦስተኛ ሆነው አጠናቀዋል። የአሸናፊነት ግምት ተሰጥቶት የነበረው አባዲ ሃዲስ ድንቅ ፉክክር ቢያሳይም በአጨራረስ ድክመት ኪፕሮፕ በሁለት ሰከንድ 58፡42 በሆነ ሰዓት ቀዳሚ መሆን ችሏል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ፍቃዱ ሃፍቱ 59:08 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ሆኖ ውድድሩን ጨርሷል። ኪፕሮፕ ያስመዘገበው ሰዓት የውድድሩ ክብረወሰን ከነበረው ሰዓት ጋር እኩል ሲሆን በርቀቱም በታሪክ አምስተኛው ፈጣን ሰዓት መሆን ችሏል። ካለፈው ረቡዕ አንስቶ በተለያዩ የዓለማችን ከተሞች ሲካሄድ በነበረው የቤት ውስጥ የዙር ውድድርም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አስደናቂ ውጤት አስመዝግበዋል። ፖላንድ ቶሩን በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮኑ ወጣት አትሌት ሳሙዔል ተፈራ የውድድር ዓመቱን መሪ ሰዓት3:35.57 በማስመዝገብ አሸናፊ ሆኗል። በዚህ ውድድር ልምድ ያለው ኢትዮጵያዊ አትሌት አማን ወጤ እልህ አስጨራሽ ፉክክር ቢያደርግም በመጨረሻዎቹ ሦስት መቶ ሜትሮች የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ሳሙዔል ተፈራ እጅ የሚሰጥ አልነበረም። በተመሳሳይ ቀንና ቦታ በሴቶች ስምንት መቶ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሃብታም አለሙ በፈጣን ሰዓት ታጅባ ያሸነፈችበት ክስተትም ያልተጠበቀ ነበር። አትሌት ሃብታም አለሙ በርቀቱ ከፍተኛ ልምድና ችሎታ ያላትን እንግሊዛዊቷን አትሌት ላውራ ሙዒርን ቀድማ በመግባት የውድድር ዓመቱ መሪ የሆነውን1:59.49 ሰዓት ማስመዝገብ ችላለች። በሳምንቱ ከተመዘገቡት ታላላቅ ውጤቶች አንዱ የሆነው በስፔን ሳባዴል በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር ገንዘቤ ዲባባ ያስመዘገበችው ነው። የዓለም የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ቻምፒዮንና የርቀቱ የቤት ውስጥም ከቤት ውጪም ክብረወሰን ባለቤቷ ገንዘቤ ዲባባ አሁንም በርቀቱ ከዓለማችን ኮከብ አትሌቶች አንዷ መሆኗን እያሳየች ትገኛለች። ገንዘቤ ምንም እንኳን ወጣ ገባ የሆነ አቋም በማሳየት ያለፈውን የውድድር ዓመት ጎልታ ባትታይም ዘንድሮ 3:59.08 የሆነ ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ሌላኛዋን ኢትዮጵያዊት አትሌት ለምለም ሃይሉን አስከትላ በመግባት ማሸነፍ ችላለች። አዲስ ዘመን የካቲት 2/2011ቦጋለ አበበ ", "passage_id": "50d23e6f5e2cf38f78d5c113c96dbab4" }, { "passage": " የዓመቱ የምርጥ አትሌቶች ሽልማት እጩዎች ከሦስት ሳምንት በፊት ይፋ ሲደረግ አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት ከምርጥ አስር እጩዎች ውስጥ መካተት አልቻለም ነበር። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይህን ክብር ደጋግመው ማግኘት ቢችሉም ባለፉት ሁለት ዓመታት በሁለቱም ፆታ ከእጩዎቹ መካከል እንኳን ሳይካተቱ መቅረታቸው አስገራሚ ነበር። ያም ሆኖ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዋናው ሽልማት በእጩነት ያልተካተቱበት አጋጣሚ በወጣቶች ወይም ከሃያ ዓመት በታች በእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ አትሌቶች በሚሳተፉበት ሽልማት ሁለት ወንዶችና አንድ ሴት አትሌት መካተት ችላለች። ከእጩነት ባሻገርም ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ሽልማቱን ማሸነፍ ችሏል። ባለፈው ቅዳሜ በሞናኮ በተካሄደው የሽልማት ስነስርዓት ላይ ኢትዮጵያውያን በኮማንደር ደራርቱ ቱሉ አማካኝነት ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ሽልማት ማግኘት ችለዋል። እኤአ 1992ና 2000 ላይ በተካሄዱት\nየባርሴሎናና የሲድኒ ኦሊምፒኮች በአስር ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎችን ያጠለቀችው ጀግናዋ አትሌት ደራርቱ ቱሉ በዓለም አትሌቲክስ\n‹‹ዘንድ የዓመቱ ምርጥ ሴት›› በሚል ሽልማት አግኝታለች። ደራርቱ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንትነት\nእየመራች ላሳየችው የላቀ አስተዋፅኦ ይህ እውቅና ተችሯታል። ደራርቱ በአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን የምክር ቤት አባል ስትሆን\nየምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆንም እያገለገለች መገኘቷ ለሽልማቱ አብቅቷታል። የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ኢትዮጵያዊ አትሌት\nሰለሞን ባረጋ የዘንድሮውን ዓመት የወጣትና ተስፈኛ አትሌቶች ሽልማት ለመጀመሪያ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል። ሰለሞን በዶሃ በተካሄደው የዓለም\nቻምፒዮና በአምስት ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ከማጥለቁ በተጨማሪ በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና አምስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።\nበውድድር ዓመቱ የዓለም ከሃያ ዓመት በታች የአምስትና አስር ሺ ሜትር ርቀቶችን 12፡53፡04ና 26፡49፡46 በሆነ ጊዜ መሪ ሰዓቶች\nማስመዝገቡ ለሽልማቱ አብቅቶታል። ባለፉት ሁለት ዓመታት በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች ድንቅ ብቃት እያሳየ የሚገኘው አትሌት ሰለሞን\nባረጋ ባለፈው ዓመትም ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ስም ዝርዝር ውስጥ መካተቱ ይታወሳል።የደቡብ ፖሊሱ ክለብ አትሌት የሆነው ሰለሞን\nባረጋ ከእድሜው ከፍ ብሎ ከታላላቆቹ ጋር በመወዳደር እያስመዘገበ ላለው ስኬት ባለፈው ዓመት ክለቡ የኢንስፔክተርነት ማዕረግ የሰጠው\nሲሆን ባለፉት ሦስት ዓመታት እያሳየ ያለው አስደናቂ ብቃት ወደ ፊት ተስፋ እንዲጣልበት አድርጓል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ወደ ታላላቅ የውድድር መድረኮች መጥቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስፖርት ቤተሰቡ\nአይን ማረፊያ የሆነው ወጣት አትሌት ሰለሞን ባረጋ ውጤቱና አስደናቂ ብቃቱ ኢትዮጵያ በቅርቡ በታላላቅ መድረኮች አረንጓዴውን ጎርፍ\nዳግም የማየት ብሩህ ተስፋ እንዳላት ማሳያ መሆኑን በርካቶች ይመሰክሩለታል። ድንቅ የሩጫ ተሰጥኦው በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች በቅርብ\nጊዜ ውስጥ ዙፋን ላይ እንደሚወጣ የስፖርቱ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ መስክረውለታል። በ2018 የውድድር ዓመት የአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊ መሆን የቻለው ሰለሞን\nባረጋ በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች የዓለም ክብረወሰንን 12፡ 43፡02 በሆነ ሰዓት ከመጨበጡ ባሻገር እኤአ 2005 ላይ ቀነኒሳ\nበቀለ በርቀቱ ካስመዘገበው ሰዓት ወዲህ ፈጣን ሰዓት ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያ በታሪክ ለመጀመሪያ\nጊዜ በሦስት ሺ ሜትር መሰናክል የብር ሜዳሊያ እንድታገኝ ያስቻለው አትሌት ለሜቻ ግርማ ከአምስቱ ተስፈኛ እጩዎች መካከል አንዱ\nበመሆን ከሰለሞን ጋር ሽልማቱን ለማሸነፍ ተፎካክሯል። ለሜቻ በውድድር ዓመቱ በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች መሪ የሆነውን ሰዓት በ8፡01፡36\nያስመዘገበ ሲሆን የኢትዮጵያን ክብረወሰንም የግሉ ማድረግ ችሏል። በዓለም ቻምፒዮናውም የወርቅ ሜዳሊያ ያመለጠው በ0ነጥብ01 ማይክሮ\nሰከንድ ተቀድሞ እንደነበረ አይዘነጋም። ከሁለቱ ኢትዮጵያን እጩዎች ጎን ለጎን ብራዚላዊው የአራት መቶ ሜትር መሰናክል ተወዳዳሪ\nአሊሰን ዶስ ሳንቶስ፣ ኖርዌያዊው አትሌት ጃኮብ ኢንግብሪትሰን፣ ዩክሬናዊው መዶሻ ወርዋሪ ማይክሃይሎ ኮክሃን በሽልማቱ ተፎካካሪ\nነበሩ። በወጣት ሴቶች ዘርፍ ከሰለሞን ባረጋ ጋር ተመሳሳይ ሽልማት ማሸነፍ የቻለችው ዩክሬናዊታ ያሮስላቫ\nማሁቺክ ናት። ይህች አትሌት በከፍታ ዝላይ የተሻለ አቅም ያላት አትሌት ስትሆን 2 ሜትር ከ04 ሳንቲ ሜትር በመዝለል የክብረ ወሰን\nባለቤት ናት። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮናም የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። ከዚህም ባሻገር አውሮፓ ቻምፒን መሆን የቻለች ጠንካራ አትሌትም\nናት። ይህን ሽልማት ለማሸነፍ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለምለም ኃይሉ ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ውስጥ ተካታ ተፎካካሪ መሆን ችላለች።\nጃማይካዊቷ ብሪታኒ አንደርሰን፣ የኢኳዶሯ እርምጃ ተወዳዳሪ ግሌንዳ ሞርጆን፣ አሜሪካዊቷ 100 ሜትር የወጣቶች ባለክብረወሰን ሻካሪ\nሪቻርድሰን የመጨረሻዎቹ ተፎካካሪዎች ነበሩ። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከእጩዎች መካከል ያልተካተቱበት የዓመቱ የምርጥ አትሌቶች ሽልማት በወንዶች\nዘርፍ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል። የማራቶን ፈርጡ ኢሉድ ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ ሁለት ፉክክሮች\nላይ ብቻ ቢታይም ያስመዘገበው ታሪክ ሽልማቱን ለማሸነፍ አብቅቶታል። ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ የለንደን ማራቶንን ክብረወሰን በማሻሻል\nበ2፡02፡37 ሰዓት ማሸነፉ ይታወሳል። ከዚህ በላይ ግን ከወር በፊት በቬና ማራቶን የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ያሳየበት\nውድድር አይዘነጋም። ኪፕቾጌ ከትጥቅ አምራች ኩባንያው ናይኪ ጋር በመሆን በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ታግዞም ቢሆን ማራቶንን ከሁለት\nሰዓት በታች ማጠናቀቅ እንደሚቻል አስመስክሯል። 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማራቶንን በማጠናቀቅ በታሪክ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆን\nቢበቃም የተመዘገበው ሰዓት በዓለም ክብረወሰንነት እንዳልተያዘ ይታወሳል።ያም ሆኖ ዓለም ዓቀፍ ሽልማቱን ከማሸነፍ አላገደውም። ባለፈው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአስር ሺ ሜትር ቻምፒዮን የሆነው ዩጋንዳዊው ጆሹአ ቺፕቴጌ\nየመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች መቀላቀል የቻለ ሲሆን፣ አሜሪካዊው ምርኩዝ ዘላይ ሳም ኬንድሪክስ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው አስራ\nሰባት ከቤት ውጪ ውድድሮች አስራ ሁለቱን በድል በማጠናቀቅ የሽልማቱ ተፎካካሪ ነበር።አሜሪካዊው የአጭር ርቀት አትሌት ኖህ ላይልስና\nኖርዌያዊው የአጭር ርቀት ኮከብ አትሌት ካርልስተን ዋርሆልም የሽልማቱ ተፎካካሪ ነበሩ። በሴቶች\nመካከል የተደረገውን ሽልማት አሜሪካዊቷ ደሊላ ሙሃመድ አሸንፋዋለች። በዓመቱ በ400 ሜትር ያሳየችው አቋም ለሽልማቱ ያበቃት ሲሆን\nአትሌቷ በሃገር አቀፍ ቻምፒዮና 52ሰከንድ ከ20ማይክሮ ሰከንድ መበመግባት ቀዳሚ ናት። በ400 ሜትር መሰናክል በራሷ የተያዘውን\nክብረወሰን 52ሰከንድ ከ16ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ብቃቷን አስመስክራለች። በ4በ 400 ሜትርም በተመሳሳይ የዓለም ቻምፒዮን ናት።\nበርዝመት ዝላይ ቬንዙዌላዊቷ ዩሊማር ሮጃስ ለመጨረሻው ዙር በመድረስ የተፎካከረች ሲሆን የአጭር ርቀት ተወዳዳሪዋ ጃማይካዊት አትሌት\nሼሊ- አን ፍራዘር-ፕረይሲ፣የማራቶን ክብረወሰንን ሰበረችው ኬንያዊት አትሌት ብርጊድ ኮስጊ፣በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በ1ሺ500\nእና10ሺ ሜትር አሸናፊ የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትልት ሲፋን ሃሰን ለመጨረሻ እጩነት ቀርበው ተፎካካሪ ሆነዋል።አዲስ ዘመን  ህዳር 16 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ", "passage_id": "d94b6faf5448369e27cea8d63ea2e5df" }, { "passage": "አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በለንደን የተካሄደውን የቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን ውድድርን ክብረ ወሰን በመስበር አሸንፏል።\nቀነኒሳ ውድድሩን 1 ሰዓት ከ 00 ደቂቃ 22 ሰከንድ በመጨረስ በበላይነት አጠናቋል።\nበዚህም ቀነኒሳ በቀለ በእንግሊዛዊው አትሌት ሞ ፋራህ ተይዞ የነበርውን የቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን ክብረ ወሰን ሰብሯል፡፡\nከቀነኒሳ ጋር ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ተጠብቆ የነበረው ሞ ፋራህ በህመም ምክንያት ከውድድሩ ውጭ መሆኑን ቀደም ብሎ ማሳወቁ ይታወሳል።\nየ5000 እና 10000 ሜትር ውድድሮች የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫይታሊቲ ቢግ ግማሽ ማራቶን ውድድር ሲሳተፍ ይህ የመጀመሪያው ነው።\nምንጭ፡- ቢቢሲ ", "passage_id": "397b2743385dafa38e60ebdf69792d8b" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ሆላንድ ሄንግሎ በተካሄደው የ5 ሺህ ሜትር ውድድር አሸነፈ፡፡ዮሚፍ ርቀቱን 13 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ከ84 ማይክሮሰከንድ በሆነ ጊዜ አጠናቋል፡፡እንዲሁም ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፈን ሐሰን በ10 ሺህ ሜትር አሸንፋለች፡፡ሲፈን ከዚህ ቀደም በፓውላ ራድክሊፍ ተይዞ የነበረውን የአውሮፓን የ10 ሺህ ሜትር ርቀት ክብረወሰንን አሻሽላለች፡፡በዚህ ርቀት ሲፈንን በመከተል ኢትዮጵያዊቷ ፀሐይ ገመቹ ሁለተኛ በመሆን አጠናቃለች፡፡", "passage_id": "9f72baff193f5f6d4313ef9085029550" } ]
ba3e4abec2bd93ec8706990178b64f4b
911397b32dad73a22118d324d3254c9e
ዋልያዎች ከዝሆኖች ገዝፈው የታዩበት ምሽት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን(ዋልያዎቹ) ከኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን(ዝሆኖቹ) ጋር ለ2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድባቸውን ሁለተኛ ጨዋታ ትናንት 10 ሰዓት ላይ ከማድረጋቸው በፊት እንደ ቅፅል ስማቸው ፍፁም የተለያየ የእግር ኳስ አቅምና ደረጃ እንዳላቸው የዓለም ሕዝብ ያውቃል፡፡ ዋልያዎቹ በዓለም ካላቸው የእግር ኳስ ደረጃና ዝና አኳያ ዝሆኖቹ እንደ ስማቸው የገዘፈ ታሪክ ይዘው በዋልያዎቹ መንደር ሲከትሙ ጨዋታውን በቀላሉ እንደሚያሸንፉ እርግጠኞች ነበሩ:: ለዚህም ዝሆኖቹ ዋልያዎቹን ባህርዳር ላይ ለመግጠም በቀጥታ ከአገራቸው እንደመጡ ምንም አይነት ልምምድ ሳይሠሩ ወደ ሜዳ በመግባት ያሳዩት ንቀት ማሳያ ነበር፡፡ እርግጥ ነው ዋልያዎቹ የዓለም ዋንጫና የቻን ማጣሪያ ጨዋታዎች ላይ ከዝሆኖቹ ያነሱ ቡድኖችን እንኳን ማሸነፍ እየተሳናቸው ተደጋጋሚ ሽንፈት እያስተናገዱ መምጣታቸው እንዲናቁ አድርጓቸዋል፡ ፡ ባለፈው ቅዳሜም በዚሁ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ ከሜዳቸው ውጪ አድርገው በማዳጋስካር 1ለ0 በመሸነፋቸው ደጋፊያቸው ሳይቀር ከዝሆኖቹ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ ተስፋ ሊጥልባቸው አይችልም፡፡ እግር ኳስ ግን እንዲህ አይደለም:: ያልተጠበቀ ውጤት ማስተናገድ፣ ያሰቡት ቀርቶ ያላሰቡት ነገር መከሰት እግር ኳስን በዓለም ሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ ካደረጉት ምክኒያቶች ዋነኛው ነው፡፡ በትናንቱ የዋልያዎቹና የዝሆኖቹ ጨዋታም የታየው ነገር ተቃራኒ ነው፡፡ እንደ ስማቸው ግዙፍ የእግር ኳስ ታሪክ ተሸክመው ወደ ሜዳ የገቡት ዝሆኖቹ በሜዳ ላይ እንቅስቃሴም ይሁን በውጤት ረገድ ከዋልያዎቹ አንስው ተገኝተዋል፡፡ በታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ በርካታ ከዋክብት ተጫዋቾችን ይዘው የመጡት ዝሆኖቹ ገና በሦስተኛው ደቂቃ ከቆመ ኳስ ግብ አስቆጥረው መምራት ሲጀምሩ በሙሉው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ዋልያዎቹ በምን ያህል የግብ ልዩነት እንደሚሸነፉ ያሰሉ ብዙዎች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ደረጃዎች የሚገኙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኖችም ሆኑ ክለቦች ሽንፈት አስተናግደው የማያውቁበት ገዳሙ የባህርዳር ስቴድየም ትናንትም ዋልያዎቹን አላሳፈራቸውም፡፡ ሱራፌል ዳኛቸው 15ኛው ደቂቃ ላይ በዝሆኖቹ የግብ ክልል አካባቢ ያገኛት ቅጣት ምት ተጨርፋ ከመረቡ ጋር በመዋሃድ ዋልያዎቹን አቻ አድርጋለች፡፡ አሰልጣኝ አብረሃም መብራቱ ዋልያዎቹን መምራት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ የተሻለ የቡድን እንቅስቃሴና ውህደት ማሳየት የቻሉት ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ለማንበርከክ መጠበቅ የነበረባቸው እስከ 24ኛው ደቂቃ ድረስ ብቻ ነበር፡፡ ጨዋታ አቀጣጣዩ ሽመልስ በቀለ በግሩም እንቅስቃሴ ኳስና መረብን አገናኝቶ ዋልያዎቹ ገና የጨዋታው አንድ አራተኛ ክፍለ ጊዜ ሳይጋመስ ከመመራት ወደ መሪነት አሸጋግሯቸዋል፡፡ በሁለተኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜም ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ቁልቁል እየተመለከቱ በድንቅ እንቅስቃሴና መስዋዕትነት ውጤቱን አስጠብቀው መውጣት ችለዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ በዋሊያዎቹ አስራ ስምንት ወራት የኃላፊነት ቆይታቸው አስራ አራት ጨዋታዎችን አድርገዋል፡፡ እንደትናንቱ አይነት ጣፋጭ ድል አጣጥመው ግን አያውቁም፡፡ አሰልጣኙ ከእነዚህ አስራ አራት ጨዋታዎች መካከል የትናንቱን ጨምሮ አራቱን በአሸናፊነት ሲወጡ፣ አምስቱን በአቻ ውጤት ደምድመዋል፡፡ ቀሪዎቹን አምስት ጨዋታዎች ደግሞ ሽንፈት አስተናግደውባቸዋል፡፡ ከዚህም በላይ ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ማንበርከካቸው እየተዳፈነ በመጣው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ላይ አዲስ ተስፋን የሚያጭር ክስተት ሆኗል፡፡ ምክኒያቱም ያንበረከኩት ኮትዲቯርን ነው፡፡ የዚህ ድል ትጉሙ ከኳስም በላይ የሚሻገር ስለመሆኑ መዘርዘር አያስፈልግም፡፡ ዋልያዎቹ ያስመዘገቡትን ያልተጠበቀ ድል ተከትሎ ወደ 2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ የማለፍ ተስፋቸው በእጅጉ ለምልሟል፡፡ ዝሆኖቹ ባለፈው ቅዳሜ በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኒጄርን በሜዳዋ አንድ ለምንም ማሸነፋቸውን ተከትሎ በሦስት ነጥብ እየመሩ ነበር፡፡ ዋልያዎቹም በምድቡ ተፎካካሪ የሚያደርጋቸውን ሦስት ነጥብ በእጃቸው አስገብተዋል:: በዚህ ምድብ የሚገኙት ማዳካስካርና ኒጄር ትናንት ምሽት ሁለተኛ ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡ ውጤታቸው ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ሰዓት ድረስ አልደረሰንም:: ይሁን እንጂ ማዳጋስካር በቅዳሜው ጨዋታ በሜዳዋ ከዋልያዎቹ ያገኘችው ሦስት ነጥብ በምሽቱ ጨዋታ ሽንፈት ቢገጥማት እንኳን በምድቡ እኩል ተፎካካሪ የመሆን እድል እንዳላት ግልፅ ነው፡፡ አዲስ ዘመን ኅዳር 10/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22835
[ { "passage": "የቤኒን ታዋቂ ጋዜጣ የሆነው ቤዢፉት የዓመቱን የቤኒን ምርጥ የስፖርት ሰው ሽልማት ዕጩዎች አስታወቀ፡፡ እንዳምናው ሁሉ የኢትዮጵያ ቡናው ግብ ጠባቂ ሃሪስተን ሄሱ ለዓመቱ ለዬሱፉ ሴሚዩ የቤኒን ምርጥ ግብ ጠባቂ እጩዎች ዝርዝር ውስጥ ከገቡ ሶስት ግብ ጠባቂዎች አንዱ መሆን ችሏል፡፡ ከሃሪስተን ጋር ተፎካካሪ ሆነው ለአመቱ ምርጥ በረኛ እጩዎች ውስጥ የገቡት ቀድሞ በለሃቭር ሲጫወት የነበረውና አሁን ደግሞ በቱርክ ለማላትያስፖር የሚጫወተው የ33 ዓመቱ ፋብያን ፋርኖል እንዲሁም በፈረንሳይ ለንዮር የሚጫወተው የ24 ዓመቱ ሳቲዩርኒን አላግቤ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ቡናው ሀሪስተን ሄሱ በ2017 ከተደረጉ ጨዋታዎች መካከል በ16 ጨዋታዎች ጎል ሳይቆጠርበት በአንደኝነት የታጨ ሲሆን የአምናው ሻምፒዮን አላግቤ በ11 እና ፋብያን በ7 ጨዋታዎችን ያለግብ በመጨረስ ይከተሉታል፡፡ከዓመቱ ግብ ጠባቂዎች ባሻገር ባሉ ዘርፎች በእግር ኳስ ልማት ኢሞሩ ቡራይማ በስፖርት ሚኒስቴር የስፖርትና የስፖርት ስልጠና ዳይሬክተር፣ ማግሏር ኦኬ የኢዩ.ኤስ.ኤስ ክለብ ፕሬዚደንት እንዲሁም ዋሃቡ አደም ሻቢ የኮቶኑ ፖርት ክለብ ፕሬዚዳንት እጩ ሆነው ቀርበዋል፡፡ከዚህ ባሻገር የዓመቱ ምርጥ ቤኒናዊ ተጫዋች፣ በአፍሪካ ውስጥ የሚጫወት ምርጥ ተጫዋች፣ ባለጥምር ዜግነት ምርጥ ቤኒናዊ ተጫዋች የሚሉ ሽልማቶች ያሉት የቤኒን ምርጥ ተጫዋቾች ሽልማት ከዛሬ ጀምሮ ለህዝብ ድምጽ ክፍት የሚሆን ሲሆን ፌብርዋሪ 26 አሸናፊው ይታወቃል፡፡\nየኢትዮጵያ ቡናው ሄሱ ባለፈው ዓመት በአፍሪካ ውስጥ የሚጫወት ምርጥ ቤኒናዊ የሚለውን ሽልማት ያገኘ ሲሆን በቱርኩ ጌንሰልበርጊ እየተጫወተ የሚገኘው የቀድሞው የዌስትብሮም ኮከብ ሰቴፈን ሴሴኞ ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ አሁን ሄሱ እጩ የሆነበትን ሽልማት ያገኘው ደግሞ ከዘንድሮ እጩዎች አንዱ የሆነው ሳቱርኒን አላግቤ ነበር፡፡", "passage_id": "8bfc7680d70462ce63e8be33fcf35dbf" }, { "passage": "ይህ ውሳኔዋም የቀሩትን ዝሆኖች ለመጠበቅ ለሚደረገው ጥረት አንድ ትልቅ እርምጃ ነው ተብሎ ተወድሷል።\n\nዝሆኖችን ለመታደግ የሚሰሩ ተቆርቋሪዎች እንደሚያምኑት 30ሺህ ያህል የአፍሪካ ዝሆኖች በየዓመቱ በአዳኞች ይገደላሉ።\n\nየቻይና መንግሥታዊ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ባለፈው ዓመት የዝሆን ጥርስ ዋጋ በ65 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል። \n\nበተጨማሪም ወደቻይና ሲገባ የሚያዘው የዝሆን ጥርስ መጠን በ80 በመቶ መቀነሱም ዥንዋ ዘግቧል። \n\nየዝሆን ጥርስ ንግድን የማገዱ ውሳኔ ይፋ የሆነው በተጠናቀቀው የፈረንጆች ዓመት ሲሆን ተግባራዊ የሆነውም በዓመቱ የመጨረሻ ዕለት ጀምሮ ነው። \n\nባለፈው ዓመት መጋቢት ወር ላይ በዝሆን ጥርስ ምርትና ንግድ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 67 ተቋማት የተዘጉ ሲሆን የተቀሩት 105ቱ ደግሞ እሁድ ዕለት እንደተዘጉ ተነግሯል። \n\nየዱር እንሰሳ ደህንነት ተከራካሪ የሆነው ተቋም ዜናውን ተከትሎ ''የዓለም ትልቁ የዝሆን ጥርስ ገበያ በሮች ሲዘጉ ማየት እጅጉን ያስደስታል'' ብሏል።\n\nየዝሆን ጥርስ ዋነኛ የመገበያያ ስፍራ እንደሆነች የሚነገርላት ሆንግ ኮንግን ግን አዲሱ ሕግ የማይመለከታት መሆኑ አሳሳቢ ነው ተብሏል። ነገር ግን ግዛቲቱ የእራሷን የዝሆን ጥርስ ንግድን የሚያግድ ሕግ ለማውጣት በሂደት ላይ መሆኗም ተነግሯል። \n\n ", "passage_id": "10ecca059eab8fb41222de9f1b37561c" }, { "passage": "በሌሎች ጨዋታዎች በነሃሴ ወር ምንም ግብ ማስቆጠር ያልቻለው የቶተንሃሙ ሃሪ ኬን አንድ ግብ ሲያስቆጥር፤ የኤቨርተኑ አዲስ ፈራሚ ሪቻርልሰን አሁንም ግብ ማስቆጠር ችሏል። \n\nነገር ግን በሳምንቱ መጨረሻ ድንቅ ብቃታቸውን ካሳዩ ተጫዋቾች መካከል የትኞቹ በጋሬት ክሩክ ምርጥ 11 ውስጥ ገቡ? \n\nግብ ጠባቂ- ጆርዳን ፒክፎርድ\n\nየሳውዝሃምፕተኑ አዲስ አጥቂ ዳኒ ኢንግስ ወደ ግብ የሰደዳትን ኳስ ያዳነበት መንገድ እጅግ አስገራሚ ነበር። የኤቨርተኑ ግብ ጠባቂ በሌላ አጋጣሚ ስህተት ሰርቶ የነበረ ቢሆንም፤ ወዲያውኑ ስህተቱን አስተካክሎ ኳሱን ግብ ከመሆን አድኖታል። \n\n• አፍሪካውያን በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውስጥ\n\n• ቀጣዩ የፕሪምየር ሊግ አሸናፊ ማን ይሆን?\n\n• ያለእድሜ ጋብቻን በእግር ኳስ የምትታገለው ታዳጊ \n\nተከላካዮች- ሼን ዳፊ፥ ስቲቭ ኩክ፤ ቤንጃሚን ሜንዲ\n\nሼን ዳፊ: ባለፈው ሳምንት የብራይተኑ አሰልጣኝ ቡድኑ በዋትፎርድ ሲሸነፍ ተጫዋቾቹን በእጅጉ የኮነነ ቢሆንም፤ በዚህ ሳምንት ማንቸስተርን ባሸነፉበት ጨዋታ ግን አስራ አንዱም ተጫዋቾች ድንቅ ብቃታቸውን አሳይተዋል ብሏል። ብዙ ሙገሳ ካገኙት ተጫዋቾች መካከል ደግሞ ተከላካዩ ሼን ዳፊ አንዱ ነበር። ሼን የማንቸስተር የፊት መስመር ተጫዋቾችን ፋታ ነስቷቸው ነበር።\n\nስቲቭ ኩክ: የበርንማውዙ የመሃል ተከላካይ ስቲቭ ቡድኑ ገና ወደ ፕሪምር ሊጉ ሳይቀላቀል ጀምሮ በታማኝነት ሲያገለግል የነበረ ተጫዋች ነው። ከዌስትሃም ጋር በነበራቸውም ጨዋታ ወጥ የሆነ አቋሙን ማሳየት ችሏል። \n\nቤንጃሚን ሜንዲ: የቤንጃሚን ሜንዲ በሲቲ ቤት ወደ ቋሚ አሰላለፍ መመለስ ከማንም በላይ የጠቀመው ለአጥቂው ሰርጂዮ አጉዌሮ ነው። ምክንያቱም ሜንዲ ጉልበቱንና ፍጥነቱን ተጠቅሞ ወደፊት በመውጣት የሚያሻማቸው ኳሶች ለአጉዌሮ ብዙ የግብ እድሎችን እየፈጠሩለት ነው። \n\nሃደርስፊልድ ላይ 6 ግብ ባስቆጠሩበት ጨዋታም ይህንኑ ነው ማድረግ የቻለው። \n\nአማካዮች- ጊልፊ ሲጉድሰን፤ ዳቪድ ሲልቫ፤ ጄምስ ማዲሰን፤ ማርኮስ አሎንሶ\n\nጊልፊ ሲጉድሰን: ይህ የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ባለፈው የውድድር ዘመን ብዙ ገንዘብ ወጥቶተበት ወደ ኤቨርተን ቢዘዋወርም፤ አስደሳች ጊዜ አላሳለፈም ነበር። በዚህ ዓመት ግን በአዲሱ አሰልጣኝ ማርኮ ሲልቫ ስር ሆኖ ድንቅ ብቃቱን የሚያሳየን ይመስላል። \n\nአይስላንዳዊው ሲጉድሰን ከሳውዝሃምፕተን በነበራቸው ጨዋታ አስገራሚ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሎ ነበር።\n\nዳቪድ ሲልቫ: ሲቲዎች ሃደርስፊልድን ስድስት ለምንም በረመረሙበት ጨዋታ ዳቪድ ሲልቫ የቡድኑን ጨዋታ ሲያቀጣጥልና የመሃሉን ስፍራ በተገቢ ሁኔታ ሲመራ ነበር። \n\nማንቸስተር ዩናይትዶች በብራይተን ከተሸነፉ በኋላ ሲቲዎች ሊያቆሟቸው የሚችሉት ሊቨርፑሎች ብቻ ይመስላሉ። \n\n• የአፍሪካ እግር ኳስ ቅሌት\n\n• የእግር ኳስ ማልያዎች ለምን ውድ ሆኑ?\n\n• የጀግና አቀባበል ለአትሌት ፈይሳ ሌሊሳ\n\nጄምስ ማዲሰን: ብራይተኖች በቻምፒዮንሺፑ በነበሩባቸው ጨዋታዎች ብዙም ብቃቱን ማሳየት ያልቻለው ማዲሰን ማንቸስተር ዩናይትድን ባሸነፉበት ጨዋታ ግን አስገራሚ ነበር። \n\nይህ የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ባለፈው ሳምንት ዎልቭስ ላይ ግብ ያስቆጠረ ሲሆን፤ አመቱ ጥሩ የሚሆንለት ይመስላል።\n\nማርኮስ አሎንሶ: የቼልሲው አሰልጣኝ ማውሪዚዮ ሳሪ ከአንቶኒዮ ኮንቴ ለየት ያለ አዲስ አይነት ቡድን ይዘው የመጡ ይመስላል። ይህ አጨዋወት ከተስማማቸው ተጫዋቾች መካከል ደግሞ አሎንሶ አንዱ ነው። በነጻነት እተጫወተ ነው። የማሸነፊያዋን ሶስተኛ ግብም ማስቆጠር ችሏል።\n\nአጥቂዎች- ካሉም ዊለሰን፤ ሰርጂዮ አጉዌሮ፤ ሃሪ ኬን\n\nካሉም ዊለሰን: የቦርንማውዙ ዊልሰን ቡድኑ ከዌስትሃም ጋር ባደረጋቸው ጨዋታዎች እስካሁን አምስት ጊዜ ግብ አስቆጥሯል። በቅዳሜው... ", "passage_id": "a61929de32fa090e4b48454f8e85f845" }, { "passage": "\nናሚቢያዊው የድሬዳዋ ከተማ አጥቂ ኢታሙና ኬሙይኔ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንደሚያመራ ያረጋገጠ ሁለተኛው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተጫዋች ሆኗል።በዓመቱ መጀመርያ ቱራ ማጂክን ለቆ ብርቱካናማዎቹን በመቀላቀል ጥሩ ዓመት ያሳለፈው ይህ ናሚቢያዊ አጥቂ በርካታ የአጥቂ አማራጮች የነበራቸው አሰልጣኝ ሪካርዶ ማኔቲን በማሳመን ሃገሩን ለመወከል ወደ መጨረሻው ዝርዝር ተካቷል። ባለፉት ሳምንታት ጉዳት ላይ የነበረው አጥቂው በዚ ሰዓት ሙሉ ጤንነት ላይ ሲገኝ ለቋሚ ተሰላፊነት ከኢስማዒልያው አጥቂ ቤንሰን ሺሎንጎ እና ሌሎች ሁለት ተጫዋቾች ጋር ይፎካከራል።በዱባይ ፖሊስ ስታድየም ዝግጅታቸው እያደረጉ የሚገኙት ናሚቢያዎች ትላንት በአቋም መለኪያ ጨዋታ ትልቋ ጋና 1-0 ማሸነፋቸው ይታወሳል።ባለፈው ሳምንት የቅዱስ ጊዮርጊሱ ኬንያዊ ግብጠባቂ ፓትሪክ ማታሲ በግብፁ አፍሪካ ዋንጫ ሃገሩን እንደሚወክል መረጋገጡ ሲታወስ ኡታሙና ኬይሙኔም ከግብ ጠባቂው ቀጥሎ ከኢትዮጵያ ክለቦች ወደ አፍሪካ ዋንጫው የሚያመራ ሁለተኛ ተጫዋች ሆኗል።ዩጋንዳውያኑ ሮበርት ኦዶንካራ እና ክሪዚስቶም ንታንቢ እንዲሁም ብሩንዳዊ ሑሴን ሻባኒ ሌሎች ወደ ግብፅ ለማምራት የመጨረሻውን ምርጫ የሚጠባበቁ ተጫዋቾች ናቸው።", "passage_id": "f3cf9db8b4aabf782f755028d4e5fd7a" }, { "passage": "በቦክሲንግ ዴይ የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታዎች አፍሪካውያን ኮኮቦች ነግሰው አምሽተዋል\nትናንት ምሽት በተጀመሩ የገና ሰሞን የቦክሲንግ ዴይ የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታዎች አፍሪካውያኑ የኳስ ክዋክብት ደምቀውና ነግሰው አምሽተዋል፡፡\nቶትንሃም ብራይተንን 2 ለ1 ባሸነፈበት ጨዋታ ኮትዲቯራዊው ተከላካይ ሰርጊ አውሬር ለእንግሊዙ አማካይ ዴሊ አሊ ያሻገራት ኳስ በመመራት ላይ የነበረውን ቶትንሃምን ለአሸናፊነት ከማብቃት ባሻገር በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ 5ኛነትን እንዲቀዳጅ አድርጋለች፡፡\nጋቦናዊው የአርሰናል የፊት መስመር ተጫዋች ፔሬ ኤምሬክ አቦሚያንግም ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በተለያዩበት ጨዋታ የአቻነቷን ጎል አስቆጥሯል፡፡ይህም ለአዲሱ አሰልጣኝ ለሚኬል አርቴታ ጅማሮ ተስፋ የሚሰጥ ነው፡፡\nጋናዊው የፊት መስመር ተጫዋች ጆርዳን አዪው ያስቆጠራት ጎል ዌስትሃምን በሴልኸርስት ፓርክ ያስተናገደው ክሪስታል ፓላስ 1 ለ 0 ከመመራት ተነስቶ 2 ለ 1 እንዲያሸንፍ አስችላለች፡፡ አዪው በጭንቅላቱ ወደ ኋላ የገጫትን ኳስ ወደ ጎል ከቀየረው ሴኒጋላዊው ቼኩ ኩዬቴ የአቻነት ጎል በኋላ አዪው 4 የዌስትሃም ተጫዋቾችን አጣጥፎ በማለፍ ነበረ በግሩም ሁኔታ የማሸነፊያዋን ጎል ያስቆጠረው፡፡\nቼልሲ ያልተጠበቀ የ2 ለ 0 ሽንፈትን ባስተናገደበት የስታምፎርድ ብሪጅ ጨዋታ ናይጄሪያዊ ዝርያ ያለው ሚካዔል ኦባፌሚ ለሳውዝሃምፕተን ጎል አስቆጥሯል፡፡ የ19 ዓመቱ አየር ላንዳዊው ኢንተርናሽናል ኦባፌሚ በ19 ዓመት ከ173 ቀናት ዕድሜው በስታምፎርድ ብሪጅ የፕሪሚዬር ሊግ ጎል ያስቆጠረ ቀዳሚው ተጫዋች ሆኗል፡፡ ይህም 2007 ወርሃ ግንቦት ላይ በ18 ዓመት ከ303 ቀኑ በብሪጅ ጎል ካስቆጠረው የኤቨርተኑ ተጫዋች ጄምስ ቫጋን በኋላ የመጀመሪያው ያደርገዋል፡፡\n\nየዓመቱ ምርጥ የአፍሪካ እግር ኳስ ተጫዋቾች ዝርዝርን የሚመሩት ሞሃመድ ሳላህና ሳዲዮ ማኔም እንደተለመደው ሁሉ በትናንት ምሽት የቦክሲንግ ዴይ ጨዋታዎች ጥሩ እንቅስቃሴ አድርገዋል፡፡ ሊቨርፑል ሌስተርን 4 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ናይጄሪያዊው ኬሌቺ ኢሃይናቾም ተሰልፎ ነበር፡፡ የአምናው ሻምፒዮን ማንችስተር ሲቲ ዎልቭስን በሚገጥምበት ጨዋታ አልጄሪያዊው ሪያድ ማህሬዝ የተሸለ እንቅስቃሴ እንደሚያደርግም ይጠበቃል፡፡\n\n\n", "passage_id": "f4a1cc651f308b06655b48cb0f700946" } ]
170de297b9a4e991684dc9fdfb0e33ba
81c3f5160a1771269bd7d585568b34cc
‹‹ ወንጀል ፈጽመው ወደጎረቤት ሀገራት የሸሹ የጁንታው አባላት የሰላም ጠንቅ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ሥራ መሠራት አለበት››-ወይዘሮ ያየሽ ተስፋሁነኝ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛ የትግራይ ክልል ተወካይ
ማህሌት አብዱል አዲስ አበባ፡- በግጭቱ ወቅት ወንጀል የፈፀሙና ሸሽተው ወደጎረቤት ሃገራት የሄዱ ወንጀለኞችና የጁንታው አባላት ተጠናክረው በመምጣት የአገር ሰላም ጠንቅ እንዳይሆኑ ከወዲሁ መሥራት እንደሚያስፈልግ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛ የትግራይ ክልል ተወካይ ወይዘሮ ያየሽ ተስፋሁነኝ አስታወቁ። ወይዘሮ ያየሽ ተስፋሁነኝ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ በማይካድራም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች ላይ በንፁሐን ላይ ጭፍጨፋ ፈፅመው ያመለጡ አንዳንድ የሳምሪ ቡድኖችም ሆኑ ሌሎች የጁንታው አባላት ተጠናክረው ተጨማሪ የሰላም ጠንቅ ከመሆናቸው በፊት መንግሥትና ህዝቡ በመተባበር የጥፋት ኃይሉን በማደን ሊይዙና በህግ ተጠያቂ ሊያደርጉ ይገባል። ‹‹እነዚህ ወንጀለኞች ሸሽተው ሄደው ተጠናክረው በመመለስ የሰላም ጠንቅ እንዳይሆኑ ከጎረቤት አገራት ጋር ባለን ጥሩ ዲፕሎማሲ ግንኙነት በመፍጠር በትብብር መሥራትና ጉዳዩንም መልክ ማስያዝ ይገባል›› ያሉት ወይዘሮ ያየሽ፤ በተለይም የአገሪቱን ሰላም ከማይሹ የውጭ ኃይሎችጋር ተቀናጅተው ችግር ከማስከተላቸው በፊት በከፍተኛ ጥንቃቄ መሠራት እንደሚገባ አሳስበዋል። በሌላም በኩል ጦርነቱን ሸሽተው የተሰደዱ ንፁሐንን ለይቶ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የማድረጉ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባዉ የተናገሩት ወይዘሮ ያየሽሽ ‹‹በዚህ ጉዳይ ላይ ትልቅ ስጋት ነው ያለኝ። መደበላለቅ የለበትም፤ የእውነት ንፁሐን የሆኑትን መለየትና ወደ አገራቸው እንዲገቡ ማድረግ ያስፈልጋል›› ብለዋል። ‹‹ጦርነት ሁልጊዜም ቢሆን አስፈሪ በመሆኑ ጦርነትን ሸሽተው የሄዱ ዜጎቻችንን በተቻለ መጠን አሳምነን መመለስ አለብን›› ያሉት ወይዘሮ ያየሽ፤ ይህም ጠላት ያልሆነውን ወደ ጠላትንት እንዳይቀር የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል። የጁንታው አመራሮች ህዝቡን “እከሌ መጣብህ፣ ተከበብክ” እያሉ ሲያሳምኑት እንደኖሩት ሁሉ በተሰደዱበት አገርም ተመሳሳይ ሊሠሩ ስለሚችሉ ይህ መልሶ የአገር ሰላም ጠንቅ እንዳይሆን ለይቶ ግንዛቤ መስጠትና መመለስ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37619
[ { "passage": "አዲስ\nአበባ፡- የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በተሰማራባቸው ቦታዎች ሁሉ ግዳጁን በውጤት የሚያጠናቅቅ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ክልሎች በዘርፉ መስራት የሚገባቸውን ስራ ባመስራታቸው የውስጥ ሠላምን የማረጋጋቱ ተግባር ለሠራዊቱ ሸክም እንደሆነ ተገለጸ። የመከላከያ\nሚኒስትሯ ኢንጂነር ዓይሻ መሃመድ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እንደገለጹት፤ ክልሎች የሚጠበቅባቸውን የቤት ስራ በአግባቡ ባለመወጣታቸው በአገሪቱ የተለያዩ አከባቢዎች አለመረጋጋቶች ይታያሉ። እነዚህን አለመረጋጋቶች ከመከላከልና ከመፍታት አኳያም የክልል ሃይሉ በሚፈለገው ልክ ባለመስራቱ የሚስተዋሉ አለመረጋጋቶች ለመከላከያ ሸክም ሆነው እንዲመጡ አድርጓል። እንደ\nኢንጂነር ዓይሻ ገለፃ፤ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉ አለመረጋጋትና ግጭቶችን ለማረጋጋት መከላከያ ሚኒስቴር እየሰራ ነው። በክልሎች በሚፈጠሩ ችግሮችም የክልል አስተዳደሮቹ ሲጠይቁ ነው የሚገባው። በገባባቸው የማረጋጋት አካባቢዎችም ችግሩ በፍጥነት ተፈትቶ ወደ ቀድሞ ሠላም ሲመለስ ይታያል። ሠላም እንዲከበር በማድረግ ሂደቱም በተሰማራባቸው ቦታዎች ሁሉ ችግሮችን ሳይፈታና ሠላሙንም ሳያረጋጋ የተመለሰበት ሁኔታ የለም። ነገር\nግን አሰራሩን ካለመገንዘብ ቶሎ እንዲገባ የሚመጡ ጥያቄዎች አሉ። “ሠራዊቱ ሕዝባዊ ባህርይውን ተላብሶ የሽምግልና ሚናም ይጫወታል” ያሉት ሚኒስትሯ፤ በዚህም ሕዝብን የማወያየትና የመፈናቀል አደጋ የገጠማቸውንም ለመደገፍ ከራሱ ራሽን ቀንሶ በመመገብ ጭምር በየካምፑ እያቆየ መሆኑንም ገልጸዋል። በተመሳሳይ\nዘረፋ ሲኖርም ተከታትሎ ሀብቱን የማስመለስ ሥራም በመሥራት ከሕዝቡ ጋር በቅርበት ለችግሮች መፍትሄ እያፈላለገም እንደሆነ ጠቁመዋል። በዚህም ሕዝቡ በተቋሙ ትልቅ አመኔታ እንዲጥልና መከላከያ ካለ ደህንነቱ የተጠበቀ እንደሆነ እንዲያምን ስላደረገው ሠራዊቱ በገባባቸው አካባቢዎች ችግሮች በቶሎ እንደሚረግቡ እንዳስቻለውም ሚኒስትሯ ጠቁመዋል። ይሁን\nእንጂ የተቋሙ ተልዕኮ አገርን ከውጫዊ ኃይልና ውስጣዊ የፀረ ሠላም ኃይል መጠበቅ መሆኑን የጠቆሙት ኢንጂነር ዓይሻ፤ በእያንዳንዱ ብሔር መካከል፣ በየቀበሌና ጉራንጉር ምን ሊከሰት ይችላል? በሚል የሚሰራ እንዳልሆነ ተናግረዋል። የውስጣዊ ሠላም መደፍረስ ሲከሰት በተቻለ መጠን ክልሎች የማረጋጋት ሃላፊነት እንዳለባቸው በመግለጽም፤ ክልሎች በዛ ደረጃ መሥራት ያለባቸውን ሥራዎች ያለመስራታቸው ደግሞ እነዚህ ሃላፊነቶች ለመከላከያ ሸክም ሆነው መምጣታቸውን ተናግረዋል።አዲስ\nዘመን የካቲት 25/2011በፍዮሪ\nተወልደ ", "passage_id": "3fff015d090633b1c7be7e655a45f8c2" }, { "passage": "እፀገነት\nአክሊሉአዲስ\nአበባ፦ ጁንታው የትግራይን ህዝብ እግር በእግር እየተከታተለ መውጪያ መግቢያ ከማሳጣት ባለፈ የጠቀመው ነገር እንደሌለ ጠንቅቆ እንደሚያውቅ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አስታወቁ።ሊቀመንበሩ\nዶክተር አረጋዊ በርሄ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳስታወቁት ፣ ጁንታው እስከ አሁን ህዝቡ በድርጅቱ ቁጥጥር ስር አድርጎ እያንዳንዷን እንቅስቃሴውን እየተቆጣጠረ መውጪያ መግቢያ አሳጥቶ ነው የኖረው ። አሁን ግን የተጎናጸፈውን ድል በመጠቀምና ነጻነቱን በአግባቡ በማጣጣም የመንግሥትን እገዛ ተጠቅሞ እራሱን ወደልማት ያስገባል።የትግራይ\nህዝብን በኢኮኖሚ በፖለቲካ ተጠቃሚ አደርጋለሁ ሲባል መጀመሪያ ሊመጣ የሚገባው ነገር ህዝቡን ማስቻል፤ መብቱን መጠበቅ፤ ተደራጅቶ እንዲንቀሳቀስ ማመቻቸት ነው ያሉት ዶክተር አረጋዊ ፣ ይህ ከሆነለት በአጭር ጊዜ ውስጥ በራሱ መንገድ ኑሮውን በማሻሻል መሰረታዊ ለውጥ ማምጣጥ እንደሚችል አስታውቀዋል።መንግሥት\nመሰረተ ልማቶችን በማሟላት፤ ለወጣቱ የሥራ እድል በመፍጠር በተለይም ደግሞ የጀመረውን ህግን የማስከበር ሥራ በመላ አገሪቱ በማድረግ የትግራይም ወጣት ሌላ ክልል ሄዶ በነጻነት እንዲሰራ በማመቻቸት በኩል ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አመልክተዋል።ጁንታው\nለትግራይ ህዝብ የማያስብ መሆኑን በዚህ ጦርነት እንኳን እራሱን ለማትረፍ ሲል በህዝብና በመንግሥት መሰረተ ልምቶች ላይ ያደረሰውን ውድመትን ማየት ይቻላል ያሉት ዶክተር አረጋዊ፣ የአክሱም የአየር ማረፊያን ጨምሮ ሌሎች በርካታ መሰረተ ልማቶችን አውድሞ መሄዱን አመልክተዋል ።ጊዜያዊ\nአስተዳደሩም እነዚህን የወደሙ መሰረተ ልማቶችን ከሚመለከታቸው ጋር በመሆኑ ወደቦታቸው መመለስ ይጠበቅበታል፤ እኛም ማህበራዊ መሰረታችን ትግራይ ክልል የሆንን ፓርቲዎች ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር በጋራ ለመስራት ባለን አቅም ሁሉ ተዘጋጅተናል ብለዋል ።በክልሉ\nሥራውን የጀመረው ጊዜያዊ አስተዳደር የህዝቡን አስከፊ ህይወት ለመለወጥ\nእንደሚሰራ ተስፋ አለኝ ያሉት ዶክተር አረጋዊ፣ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ክልሉን እንደገና ለመገንባትና ከዚህ በፊትም አጥቶት የነበረውን\nመሰረተ ልምት ለማሟላት እንደ ፓርቲ ህዝቡን በማስተባበር ሌሎች አስፈላጊ ድጋፎችንም በማድረግ እንደሚሳተፉም አስታውቀዋል።የትግራይ\nክልል ከዛሬ 46 ዓመት በፊት ጀምሮ በጦርነት እጅግ የተጎዳ አካባቢ ነው፤ ህዝቡም በእርዳታ ስንዴ የሚኖር የተስተካከለ የመጠጥ ውሃ እንኳን ያላገኘ ነው ያሉት ዳክተሩ፣ ጁንታው በስሙ እየነገደ የሚያጋብሰውን ሃብት ስለተመቸውና እራሱን አንደላቆ እንዲሁም ልጆቻቸውን እጅግ በተቀናጣ ምቾት ውስጥ ማኖር ስለቻሉ ብቻ ስለ ህዝቡ ደንታ ቢስ ሆነው መቆየታቸውን ጠቁመዋል።ይህ\nመሆኑ ደግሞ ሌላውም የአገሪቱ ህዝብ የእነሱን መንደላቀቅ ሲያይ ህዝቡም በዛው ልክ ተመችቶት የሚኖር እየመሰለው መቆየቱን ጠቁመው፣ ነገሩ ሁሉ የተገላቢጦሽ ነው። የገዢዎቹና የህዝቡ ኑሮ ሰማይና ምድር ነው ። ይህንን ማስተካከል ደግሞ የቀጣይ የቤት ሥራችን ይሆናል ብለዋል።የህግ\nማስከበሩ ጉዳይ ተጠናክሮ እየቀጠለ ነው ያለው ያሉት ዶክተር አረጋዊ ፣ ጁንታው ሁሉም በሚባል መልኩ ከአዲስ አበባ ሸሽተው እንደሄዱት ሁሉ መቀሌ ላይም ሴራ ሲጠነስሱ ከርመው በአሁኑ ወቅት እዛም ስላልሆነላቸው በመሸሸና የሚደበቁበትን ጥግ በመፈለግ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።የመከላከያ\nኃይላችንም ከህዝቡ ጋር እየተባበረ እነሱን ይዞ ለፍርድ ለማቅረብ አደን ላይ ነው ። የእነሱ ቡድን አባል የሆነችው ሴትም እጇን ሰጥታለች፤ በቀጣይም ሁሉም እጅ ይሰጣሉ ፤ አንሰጥምም ቢሉ ከመሞት ሌላ አሁን ላይ ምንም አማራጭ እንደሌላቸው ጠቁመዋል።“ የጁንታው\nቀንደኛ አባላት በቁጥር ትንሽ ቢሆኑም በርካታ የጥቅም ተጋሪዎች፣ አገልጋዮች፣ ተባባሪዎች እንዲሁም ቤተሰቦችና ታማኞች በትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን በመላ አገሪቱ አሉ፤ ይሁን እንጂ ህዝቡ ማን ምን እንደሆነ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ የባሰበትን ለጸጥታ አስከባሪ አሳልፎ በመስጠት ሌላውን ደግሞ በራሱ መንገድ አርፎ እንዲቀመጥ በማድረግ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። እኛም እንደ ፓርቲ በተለይም ሌቦቹና ዘራፊዎቹ ህግ ፊት እንዲቀርቡ ለማድረግ ከፍተኛ የሆነ ትብብርን ለማድረግ ተዘጋጅ ተናል” ብለዋል።አዲስ\nዘመን ህዳር 28/2013 ", "passage_id": "0fe83c1bf1490f10892e71df04a6b9a9" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ህዳር 22 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የጁንታው ህወሓት ጥፋት አስፈጻሚ ርዝራዦች ከጥፋታቻው በመታቀብ በአጭር ቀናት ውስጥ እጃቸውን ለዞኑ ኮማንድ ፖስት እንዲሰጡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሳሰቡ።", "passage_id": "9ac9371341cd0b9d059cf49ec2a6f33e" }, { "passage": "ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋዊ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት “የጁንታው ፀሐይ እየጠለቀች ነው። ይሄንን መርዶ ጁንታው በቁሙ ተረድቶታል። አሁን የሚይዘውን የሚጨብጠውን የሚያጣበት ጊዜ ነው” ብለዋል፡፡በጣዕር መንፈስ በየቦታውየመጨረሻውን የጥፋት ድግስ ይደግስ ይሆናል። ስለዚህም ሕዝቡ በንቃትና በተደራጀ መንገድ አካባቢውን እንዲጠብቅ አደራ እላለሁ ነው ያሉት።ከዚሁ ጋር በተያያዘ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወገኖቻችን በየአካባቢያችን\nምንም ዓይነት አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይደርስባቸው ሁላችንም የወንድሞቻችን ጠባቂ እንሁን ብለዋል።<< የኢትዮጵያ ጠላት ስግብግቡ ጁንታ ነው። የትግራይ ሕዝብ እንደሌላው ሕዝብ በጁንታው መከራ ያየ ሕዝብ ነው። ጁንታው ለፍርድ እንዲቀርብ የትግራይም ሕዝብ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር አብሮ እየተዋጋ ነው።አካባቢዬን እጠብቃለሁ፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ የመከራ ቀንበር እሰብራለሁ። ጁንታውን ለፍርድ ማቅረብም ቃልኪዳናችን ነው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡", "passage_id": "5dfd61027d895f503554f4558aee889d" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ህዳር 20 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) መቐለ መሽጎ በነበረው የህወሓት ጁንታ መወገድ ዋነኛ ተጠቃሚ የሚሆነው የትግራይ ህዝብ ነው ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን ገለጹ።ርዕሰ መስተዳድሩ የሃገር መከላከያ ሠራዊት መቐለን በመቆጣጠሩ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።ይህንኑ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ህወሓት ለ27 ዓመታት በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ተቀምጦ እርስ በእርስ ሲያጋጭ ነበር ብለዋል።ይህን ለማሳካት የሀገሪቱን ሕዝቦች በብሄር በመከፋፈልና ግጭት በመቀስቀስ ስልጣኑን ለማስቀጠል ከፍተኛ ማህበራዊ ቀውስ እንዲፈጠር ማድጉን አመላክተዋል።በጠረፍ አካባቢ የሚገኙ ክልሎችን ደግሞ በሞግዚት በማስተዳደር የተፈጥሮ ሃብታቸውን መዝረፉን ያስረዱት አቶ አሻድሊ፥ ክልሎች በአግባቡ እንዳይለሙም አድርጓልም ነው ያሉት።ህወሓት በትጥቅ ትግል ያካበተውን ሴራ ለውጡን ለማደናቀፍ እንደተጠቀመበት አመልክተው በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች ንጹሃን እንዲጎዱና ንብረት እንዲወድም አድርጓል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።", "passage_id": "d8a536b0b230eb78423f2881b01d9a6d" } ]
314735bbbf3d25aa319ebdccf89aceb8
ab446527b425e60670a5afe4046312f1
“አሁን ያለችው ትግራይ 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት ናት ” -አቶ ሊላይ ኃይለማርያም፣ የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት ከፍተኛ አስተዳደር
አዲሱ ገረመው አዲስ አበባ፡- አሁን ላይ ያለችው ትግራይ የአምባገነኑ ጁንታ እንቅስቃሴ እምብዛም የማይታይበት 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት መሆኗን የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ተናገሩ። የህወሓት ጁንታ ከአሁን በኋላ እንደማይመለስና ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ገሀነም መውረዱን በመገንዘብም ደጋፊዎችና አባሎቻቸው ወደ ህዝባቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲመሰርቱና በጋራ አገር ግንባታ ውስጥ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል። አቶ ሊላይ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ አሁን ትግራይ በአጠቃላይ 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት ሆናለች። የአምባገነኑ ጁንታ እንቅስቃሴ የሚታይበት ሁኔታ ብዙም የለም። አውሮፕላንን ጨምሮ ትራንስፖርት ከጫፍ እስከ ጫፍ ይንቀሳቀሳል። መብራት እስከ አዲግራት እየሠራ ሲሆን፤ በዚህ ሳምንት ዓደዋና አክሱም ይገባል። አብዛኛው ከተሞችም መብራት ያገኛሉ። የውሃና የኔትዎርክ አገልግሎትም እየተዳረሱ ነው። በሚቀጥለው ሳምንትም የባንክ አገልግሎት በሰፊው ይጀመራል። መቀሌም በጥሩ እንቅስቃሴ ውስጥ ነው ያለችው። ወደ ቀደመ መልኳ ተቀይራለች።የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ አንጻር መቶ በመቶ እንዲከፈቱ ተደርገዋል። በሰለማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሰው ሁሉም ሰው ወደ ሥራ ገበታው ገብቷል። ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሥራ ያልገቡ ሠራተኞች ላይ በአገሪቷ ህግ መሠረት ዕርምጃ ይወሰዳል። ይሄ ደግሞ የተሾሙት ካቢኔዎች ኃላፊነት ነው። ትጥቅን የማስፈታት እንቅስቃሴውም በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል። ታጥቆ የነበረው ትጥቅ በየቦታው እየተፈታ ነው።ትጥቅን በማስፈታት ረገድ “ከሞላ ጎደል ህዝቡ ሳንጠይቀው ነው እየመጣ ትጥቅ እያስረከበ ያለው” ያሉት አቶ ሊላይ፤ የህወሓት ጁንታ ከጩቤ ጀምሮ እስከ ከባድ ብረቶች ከ200 ሺ በላይ ትጥቅ ያስታጠቀ ቢሆንም እነዚህ እየተመለሱ መሆኑን አስረድተዋል። አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊየን ታጣቂ ያለበት ክልል እንደመሆኑ ትጥቅ የማስፈታት ሂደቱ ቀላል እንቅስቃሴ እንዳልሆነና በአንድ ቀን የሚመለስ ሳይሆን ጊዜ የሚጠይቅ መሆኑን በመጠቆምም፤ ህዝቡ ግን በፈቃደኝነት እየመለሰ መሆኑንም ተናግረዋል። ይህ ተግባር ቀጣይነት ያለው መሆኑን እና በዚህ ረገድ መከላከያው እየረዳን ስለሆነ መከላከያ ባለበት ቦታ እየሄዱ ቀበሌ በተመሠረተበት በየወረዳው፣ በየዞኑ በየከተማው አጥጋቢ በሆነ መልኩ እየመለሱ መሆኑንም አብራርተዋል። እንደ አቶ ሊላይ ማብራሪያ፤ ከሰብዓዊ ድጋፍና የመድኃኒት አቅርቦት ጋር ተያይዞ በተለይ በጤና አገልግሎት ባለው ሂደት የፌዴራል መንግሥት በአቅሙ እየረዳ ነው። በቀጣይም ብዙ የሚፈለግ ነገር አለ። ምክንያቱም ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች በጁንታው ተዘርፈዋል። ጁንታው ሲሸሽ ዘርፎ ነው የሄደው። በዚህ ረገድ ብዙ መሥራት ያለብን ነገሮች አሉ። ከዚህ ባለፈ ግን የሰብዓዊ ድጋፉም እየተከፋፈለ ሲሆን፤ በቀጣይ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት በተቀላጠፈና በተጠና መንገድ እየተሠራ ነው። ይሄን ተግባር እንዲፈጽም ኃላፊነት የተሰጠው ጊዜያዊ አስተዳደርም ከተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ዘመናዊ አመለካከት ባላቸው ሰዎች ጋር በመሆን የተዋቀረ ሲሆን፤ የአረና፣ የትዴፓና የብልጽግና ፓርቲዎች በዚህ ውስጥ ከተካተቱት መካከል ናቸው። የፓርቲ አባል ያልሆኑ ግለሰቦችም አሉ። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዕድሜም ስድስት ወር እንደመሆኑ፤ በዚህ ስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ህግና ስርዓትን በማስከበር ትግራይን ማረጋጋት ዋና ተግባሩ ይሆናል። ስድስት ወሩ ካለቀ በኋላ ምርጫ ማካሄድ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወዳድረው ምርጫ እንዲያደርጉም ይደረጋል። በዚህም ከቀበሌና ወረዳ ጀምሮ ባለው ሂደት ነፃ ምርጫ ይደረጋል። ሰው የፈለገውን እንዲመርጥ ይደረጋል። እንደ ከዚህ ቀደም በካድሬ የሚመራ ሳይሆን በአገር ሽማግሌ እንዲመራ ነው የሚፈለገው። ነፃ በሆነ መንገድ ሰው በወንዙ ልጅ ይመረጣል፤ ይዳኛልም። የጊዜያዊ አስተዳደሩም አቋም ይሄው ነው። ማንም የፖለቲካ ፓርቲ የፈለገውን አመለካከት ይዞ በነፃ በትግራይ በሠላማዊ መንገድ መንቀሳቀስ ይችላል። ህልማችን ክልሉ የዴሞክራሲ ምልክት የሠላም ምልክት የልማት ምልክት እንዲሆን ስለምንፈልግ ምርጫው ፍጹም ሠላማዊ፣ ህዝባዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ይካሄዳል፤ በማለት አቶ ሊላይ ገልጸዋል።በመጨረሻም “የኢትዮጵያ ህዝብ ለትግራይ ህዝብ የሚያደርገውን ትብብር ማጠናከር አለበት። በዚህም አጋጣሚ የህወሓት ጁንታ ከአሁን በኋላ እንደማይመለስና ፍጹም ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ገሀነም እሳት መውረዱን ለደጋፊዎችና ለአባሎቻቸው እየገለጽኩኝ፤ ወደ ህዝባቸው ተመልሰውና ተቀላቅለው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲመሠርቱ እና እነርሱ ላለፉት 46 ዓመታት ያወደሙትን አገር እንደገና በጋራ እንድንገነባ ጥሪ አቀርባለሁ” በማለት አቶ ሊላይ መልዕክት አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37618
[ { "passage": "የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ\n\nየአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ ማዕከል ያወጣው መግለጫ፤ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከተቋቋመ በኋላ በተለያዩ አካባቢዎች በአስተዳደሩ አባላት ላይ በህወሓት በተፈጸሙ ጥቃቶች 22 ሰዎች መገደላቸውን አመልክቷል። \n\nበተጨማሪም በአራት የጊዜያዊው አስተዳደር አባላት ላይ በተፈጸመባቸው ጥቃት ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ላይ እንደሚገኙ ማዕከሉ ያወጣው መግለጫ ጠቅሷል። \n\nበዚህም ሳቢያ በአጠቃላይ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 46 የጊዜያዊው አስተዳደር ሲቪል አባላት በህወሓት ኃይሎች ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ተገልጿል።\n\nመግለጫው ጨምሮም በክልሉ መረጋጋት በማምጣት ሕዝቡ ወደ መደበኛው ሕይወት እንዲመለስ ለማድረግ ጥረት በማድረግ ላይ ባሉት የጊዜያዊ አስተዳደሩ አባላት ላይ ቡድኑ ከሚፈጽመው ጥቃት ባሻገር በንብረት ላይም ውድመት መድረሱን ጠቅሷል። \n\nመግለጫው በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ውስጥ በህወሓት ኃይሎች ጥቃት ተፈጸመባቸው ያላቸውን የጊዜያዊውን አስተዳደር አባላት ቁጥር በዝርዝር ያወጣ ሲሆን፤ ከፍተኛው ግድያ የተፈጸመው በሰሜን ምሥራቅ ክፍል ውስጥ ዘጠኝ ሰዎች የተገደሉበት መሆኑን አመልክቷል። \n\nከዚህ ባሻገርም በማዕከላዊ ዞን 6፣ በደቡብ 3 እንዲሁም በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ አንድ አንድ የጊዜያዊው አስተዳደር አባላት ተገድለዋል ይላል መንግሥት ያወጣው መግለጫ።\n\nበተጨማሪ ደግሞ በደቡብ ዞን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የጊዜያዊው አስተዳደር አባላት የታፈኑ ሲሆን ቁጥራቸውም ዘጠኝ ነው። በሌሎች ቦታዎች ደግሞ በደቡብ ምሥራቅ 5፣ በማዕከላዊ 4 እና በምሥራቅ 2 የአስተዳደሩ አባላት ታፍነዋል ተብሏል። \n\nከጊዜያዊ አስተዳደሩ አባላት መካከልም በህወሓት ተፈጸመባቸው በተባለው ጥቃት አራት ሰዎች በተለያዩ ዞኖች ውስጥ የመቁሰል ጉዳት እንደደረሰባቸው መግለጫው አመልክቷል። \n\nለሦስት አስርት ዓመታት ያህል በኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግሥት ሥልጣን ላይ ከፍተኛ ሚና የነበረው ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ከሦስት ዓመታት በፊት በአገሪቱ የመጣውን የአመራር ለውጥ ተከትሎ ዋነኛ ማዕከሉን ትግራይ ውስጥ አድርጎ ቆይቶ ነበር።\n\nህወሓት ከማዕከላዊው መንግሥት ጋር የነበረው አለመግባባት የአገራዊውን ምርጫ መራዘም ተከትሎ በትግራይ ክልል ውስጥ በተናጠል ባካሄደው ምርጫ ሳቢያ የፌደራል መንግሥቱ በወሰደው እርምጃ የበለጠ ተባብሶ መቆየቱ ይታወሳል። \n\nጥቅምት 24/2013 ዓ.ም የህወሓት ኃይሎች ትግራይ ውስጥ በነበረው የፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት ላይ የፈጸሙትን ጥቃት ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ካዘዙ ከሳምንታት በኋላ ህወሓት ከ30 ዓመታት በላይ ከተቆጣጠረው የክልሉ የሥልጣን መንበር ተወግዷል።\n\nበዚህም በርካታ ከፍተኛ አመራሮቹ በውጊያዎች ውስጥ መገደላቸውና በፌደራል መንግሥቱ መያዛቸው አይዘነጋም። \n\nቢሆንም ግን ቡድኑ አሁንም ድረስ በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ ጥቃት እየፈጸመ እንደሆነ ከዚህ በፊት የሚወጡ መረጃዎች ያመከቱ ሲሆን፤ አሁን ከመንግሥት በኩል የወጣው ቡድኑ የፈጸማቸው ግድያዎችና ጥቃቶችን የሚያመለክተው መረጃ ይህንኑ ያረጋግጣል።\n\nከጥቂት ሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይን (ህወሓት) የሽብር ቡድን ብሎ መሰየሙ ይታወሳል። \n\n ", "passage_id": "0530b12358104085b939de7c5be61a07" }, { "passage": "የፓርቲው ሊቀመንበር ከዋልታ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፣ በሀገር ላይ ክህደት የፈጸመው ጁንታ ከምንም እና ከማንም በላይ ሲጨቁነው እና ሲዘርፈው የኖረው የትግራይን ህዝብ ነው፡፡በትግራይ ክልል የነበሩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህገ መንግስቱ በሚፈቅድላቸው መንገድ በክልሉ መንቀሳቀስ እንዳይችሉ ጽንፈኛው የትህነግ ቡድን አፈና ሲያደርግባቸው መቆየቱን የገለጹት ዶ/ር አረጋዊ፣ አሁን ላይ ግን ምቹ መደላድል ይፈጠራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል፡፡የትግራይ ተወላጅ የሆኑት አቶ ዮሃንስ ሃይሉ በበኩላቸው፣ አስፈላጊ በሆነው መንገድ ሁሉ በክልሉ ከተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸው፤ የህወሓት ጁንታው ቡድን ላለፉት ረጂም አመታት ሲጨቁነው ከቆየው ህዝብ ውስጥ ተሸሽጎ እንዳለና ይህን ጁንታ በማጋለጥ የትግራይ ህዝብ አኩሪ ታሪክ ሊሰራ እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደሩ እያከናወነ ያለው ስራ የሚደነቅ እንደሆነና በቀጣይም ጠንከር ያሉ የቤት ስራዎች የሚጠብቅ በመሆኑ እያንዳንዱ የትግራይ ተወላጅ ከገዜያዊ አስተዳደሩ ጎን ሊቆም እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡ከሁለት አስርት አመታት በላይ በኢትዮጵያ እና በትግራይ ህዝብ ጫንቃ ላይ ተቀምጦ እንደካንሰር ራሱን በማስፋፋት ህዝቡን ሲበዘብዝ የኖረው የህወሓት ዘራፊ ቡድን ህዝባዊ በሆነው የመከላከያ ሰራዊት ድል ተደርጎ የትግራይ ህዝብ የሰላም አየር መተንፈስ ከጀመረ  ሳምንታት ተቆጥሯል፡፡መንግስት በክልሉ ያቋቋመው ጊዘያዊ አስተዳደርም ህበረተሰቡን በማወያየት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ በራስ ወዳዱ ጁንታው ቡድን የተበላሸውን የመልካም አስተዳደር ችግር ለማስተካከል ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡(በሜሮን መስፍን)", "passage_id": "46abd6d1340df968a88aa0e681c641d8" }, { "passage": "የኢትዮጵያ መንግሥት በሙስናና ሰብዓዊ መብት ጥሰት ጠርጥርያቸዋለሁ ያላቸውን ሰዎች በቁጥጥር ሥር እያዋለ ይገኛል ይህ ጉዳይም መነጋገርያ ሆኗል።በዚህ ጉዳይ አስመልክቶ የአቋም መግለጫ ያወጣ የትግራይ ክልል መንግሥት የክልሉ ህዝብና መንግሥት የህግ ልዕልና እንዲሰፍን አበርትተው ይሰራሉ ብሏል። እንዲሁም በሙስናና ሰብዓዊ መብት ጥሰት እየታየ ያለ ሁኔታ አንድ ብሄር መሰረት እንዳያደርግ እንታገላለን ሲል ገልፅዋል፡፡በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስና ስትራቴጂካዊ ጥናት አስተማሪ አቶ ሰይፈ ኃይሉ እየተወሰደ ያለው እርምጃ የሕግ ልዕልና ከማስከበር ይልቅ ፖለቲካዊ መልክ የያዘ የትግራይ ሊህቃን ለማጥፋት ያለመ ነው ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።የዓረና ለሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ብሔር መሰረት ያደረገ ነው ብለህ ለመናገር የሚያስደፍር አይደለም ብለዋል።ሰብ ሕድሪ የተባለ ሲቪል ማሕበረሰብ በበኩሉ በጥናትና ሚዘናዊ የሆነ የህግ ተጠያቂነት መኖር አለበት ብለን እናምለን በማለት የገለፀ ሲሆን ሆኖም ግን በአሁኑ ግዜ በአገሪቱ በህግ ልዕልና ስም የትግራይ ተወላጆች የማዳከም ሥራ እየተሰራ መሆኑን እንደሚገነዘብ አስታውቋል። ", "passage_id": "2cb158fe8140007fe8d7710813cf783a" }, { "passage": "የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የአገሪቱን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ በተመለከተ ሰኞ የካቲት 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ለክልሉ ቴሌቪዥን በሰጡት አጭር አስተያየት፣ ‹‹ሕገ መንግሥቱ እየተጣሰ ትዕግሥት የሚባል ነገር ሁሌ አይሠራም፣ ዕርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል፤›› አሉ። በአገሪቱ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ ሕገ መንግሥቱን የመጣስና በትግራይ ሕዝብ ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች የሚሰነዘሩበት እንደሆነ ገልጸው፣ የፖለቲካ ሥርዓቱ የጋራ እንደ መሆኑ መጠን ሁሉም ሊጠብቀው እንደሚገባ አስረድተዋል።ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን አንዱ የሚጠብቀው አንዱ የሚጥሰው መሆን እንደሌለበትም ተናግረዋል።ሕገ መንግሥቱ እየተጣሰ ትዕግሥት የሚባል ነገር ሁሌ ስለማይሠራ ዕርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ብለው፣ እሱ እንዳይሆን (ወደ ዕርምጃ እንዳንገባ) ግን ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። የትግራይ ክልልን የሚያስተዳድረው ገዥው ፓርቲ ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ማዕከላዊ ኮሚቴ የካቲት 11 ቀን 2011 ዓ.ም. የተከበረውን 44ኛ የምሥረታ በዓሉን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫም፣ ድርጅቱና ደጋፊዎቹ የምሥረታ በዓሉን የሚያከብሩት በኢትዮጵያ የተጀመረውና መላው ዓለም የመሰከረለት የለውጥና የዕድገት ጉዞ ወደ ኋላ እየተቀለበሰ፣ ብርሃን ማየት የተቻለበት የብልፅግና ጉዞ ወደ ሥጋትና ጭንቀት እየተቀየረ ባለበት ወቅት እንደሆነ አስታውቋል። ለተጠቀሰው ችግርም የኢሕአዴግ አመራር ውስጥ የተፈጠረ አለመግባባትና የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት እንደሆኑ ያመለክታል። ‹‹የዚህ ሁሉ ችግር መሠረታዊ ምክንያት፣ በኢሕአዴግ አመራር ውስጥ እየተንከባለሉ የመጡ የጥገኝነት አስተሳሰብና ተግባር ወደ ከፋ ደረጃ በመድረሱ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። ከዚህ ቀደም በኢሕአዴግ አመራር የተጀመረውን በጥልቀት የመታደስ ሒደት በጋራ በተቀመጠው አቅጣጫ ባለመሄዱና በመኰላሸቱ፣ እንዲሁም የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት በመኖሩ ጭምር ነው፤›› ሲል መግለጫው ያትታል። በአገሪቱ በአሁኑ ወቅት ሰላምና መረጋጋት እየጠፋ መሆኑን፣ የሕዝቦች መሠረታዊ ፍላጎቶች የሆኑትን ልማትና ዴሞክራሲ ወደ ጎን በመባላቸው የተጀመረው ፈጣን፣ ተከታታይና ፍትሐዊ የልማት ዕድገት ችግር ውስጥ በመውደቅ ላይ ነውም ብሏል።‹‹በስመ ለውጥ ለአገራቸው ክብርና ሉዓላዊነት መረጋገጥ ዕድሜ ልካቸውን የደከሙና የለፉ የሚረገሙበትና የሚብጠለጠሉበት፣ በአገሪቱ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በዜጎች ላይ የተለያዩ በደሎችና ግፍ የፈጸሙ፣ እንዲሁም የአገራቸውን ሉዓላዊነት አሳልፈው የሰጡ ብቻ ሳይሆን፣ ከሌሎች የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር አብረው አገርና ሕዝብ የወጉ የሚመሠገኑበትና ክብር የሚሰጥበት የክህደት ዘመን ላይ ደርሰናል፤›› በማለት ሕወሓት በመግለጫው ትችቱን ሰንዝሯል። ይሁን እንጂ የአገሪቱ ሁኔታ ሕወሓት ካወጣው መግለጫ በተቃራኒ እንደሆነ በርካቶች ይገልጻሉ። ከምንጊዜውም የተሻለ ዴሞክራሲ የሰፈነበት፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የቆሙበትና ቀደም ሲል ለተፈጸሙ ጥሰቶችም ፍትሕ የተሰጠበት መሆኑን የአገሪቱ የፖለቲካ ልሂቃን፣ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የተለያዩ የውጭ መገናኛ ብዙኃንና ዓለም አቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ በይፋ እየተናገሩ ናቸው። በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉ ግጭቶችና የዜጎች መፈናቀል መኖር እርግጥ ቢሆንም፣ የፖለቲካ ሽግግር ከዚህ የፀዳ ሊሆን እንደማይችል ነገር ግን ይህ ችግር እየደበዘዘ መሄድ እንዳለበትና በአሁኑ ወቅትም መረጋጋት መኖሩን ያስረዳሉ። ሕወሓት በፖለቲካ ማዕከሉ ላይ የነበረው ተፅዕኖ በመቀነሱ የመገፋት ስሜት ሊጫነው እንደሚችል፣ ይኼንንም የሚያባብሱ የፖለቲካ ትግሎች በኢሕአዴግ ውስጥ መቀጠላቸው በግልጽ የሚታይ ቢሆንም፣ ጉዳዩን ከሕዝብ ጋር ማገናኘት ስህተት እንደሆነ በርካታ የፖለቲካ ልሂቃን በተለያዩ መድረኮች በተደጋጋሚ የሚያነሱት ሐሳብ ነው።", "passage_id": "205274361149b450b24b226ead0712e9" }, { "passage": "ዶ/ር ደብረጽዮን ካነሷቸው ነጥቦች መካከል ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል በትግራይ ላይ ብዙ መረባረብ ቢኖርም ሰላማችንን ለመጠበቅ በመቻላችን ልንቋቋመው ችለናል ብለዋል።ትግራይ ውስጥ በጊዜ ብድር ያለመክፍል ችግር እንዳለም አንስተዋል። ለአርሶ አደሮች ከፌዴራል መንግሥት ብድር የሚሰጠው በክልል ዋስትና በመሆኑ በጊዜ አልተከፈለም በሚል ፌደራል መንግሥት ለትግራይ ክልል ከሚመድበው ባጀት 200 ሚልዮን ብር ቆርጧል። ገናም እንደሚቀንስ ተናግሯል ብለዋል ዶ/ር ደብረጽዮን። ዶ/ር መሐሪ ታድያ መንግሥት ራሱ ከቻይና የተበደረውን ብድር መክፈል አቅቶት የክፍያ ማራዘምያ እየጠየቀ ባለበት ሁኔታ የትግራይ ገበሬ ብድሩን ባለመክፍሉ የክልሉን ባጀት መቁረጥ ተገቢ አይደልም ብለዋል።ዶ/ር መሐሪ ረዳኢ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ መምህር ናቸው። አቶ ገብሩ አስራት ደግም የዓረና ትግራይ ለሉዓላዊንትና ለዲሞክራሲ እንዲሁም የመድረክ አመራር አባል ናቸው። ", "passage_id": "6607fe8ed177a5252d9606986cf1f5fc" } ]
f440859b65252ea34d1a208f1088a179
605e6f5ae9e0f1d520641928b1d0bbec
በሦስት አገራት 800 ሺ ሕፃናትን ተጠቃሚ የሚያደርግ የትምህርት ፕሮጀክት ሊተገበር ነው
አስመረት ብስራት አዲስ አበባ፡- በሦስት የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ተግባራዊ የሚደረግ ከሦሰት እስከ አስራ ሁለት ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ 800 ሺህ ሕፃናትን በጨወታ መልክ ለማስተማር የሚያስችል ለአምስት ዓመታተ ተፈፃሚ የሚሆን ፕሮጀከት ስምምነት ተፈረመ።የፕሮጀክቱ መክፈቻ የፊርማ ስነ ስርዓት ትናንት በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል በተከናወነበት ወቅት የፕሮጀክቱ ዳይሬክተር ማረቲን ኦምኩባ እንዳስታወቁት፤ ፕለይ ማተር በሚል ስያሜ በኢትዮጵያ፥ በታንዛኒያና በዩጋንዳ የሚገኙ በስደተኛ ካምፖች ውስጥ የሚኖሩ ሕፃናት ፤ ብሎም በስደተኛ ካምፖች አካባቢ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ልጆችን ያጠቃለለ እየተጫወቱ የሚማሩበት ዓይነት የትምህርት ስርዓት ለማዳረስ የሚያስችል ፕሮጀክት ነው።ይህ ፕሮጀክት ከሊጎ ፋውንዴሽን በተገኘ መቶ ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ተፈፃሚ የሚደረግ መሆኑን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፤ በሀገራችን በአፋር፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በጋምቤላ በሶማሌና በትግራይ ክልሎች ተፈፃሚ እንደሚሆንም ተናገረዋል።ሕፃናት በባህሪያቸው ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ፤ የተለያዩ የጦረነትና በችግር ሁኔታ ውስጥ ሲቆዩ የተለያዩ የስነልቦና ጫናዎች ሊገጥሟቸው እንደሚችሉ የተናገሩ ሲሆን፤ በቅድመ መደበኛና በመደበኛ ደረጃ የሚገኙ ሕፃናት በስነልቦና፤ በጠቅላላ እውቀት በአዕምሯዊና በአካላዊ ዕድገት ሊደግፋቸው የሚችል የትምህረት ስርዓት መሆኑ ተጠቁማል።እንደ ዳይሬክተር ማረቲን ገለፃ፤ ሕፃናትን በተለያዩ የጨዋታ መልኮች በማስተማር አወንታዊ ተፅእኖዎቹ በጣም ከፍተኛ መሆኑን አስረድተው፤ በመማር ማስተማር ስርዓቱ ውስጥ ቤተሰቦቻቸው፤ የተለያዩ በቅርበት የሚገኙ አካላትና በስደተኛ ካምፑ ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ አገልገሎት ሰጪዎች ተሰታፊ የሚሆኑበት ነው።የፕሮጀክቱ መጨረሻ ላይ እንደ ግብ የተቀመጠው በመማር ማስተማሩ ልጆቹ የተሻለ የትምህርት አቅም መገንባታቸው ታይቶ እንደየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ በመቀያየር ውጤት ላይ መድረስ መሆኑን ጠቁመዋል። በፕሮጀክቱ መክፈቻ እና የፊርማ ሥነስርዓት ላይ የስደተኛ ጉዳዮች ተወካይ፣ ከትምህርት ሚኒስቴር የተወከሉ ግለሰብና፣ በፕሮጀክቱ ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37629
[ { "passage": "የሴቶች ትምህርት የህጻናት ጋብቻን ለመቀነስ ረድቷል\n\nእንደዩኒሴፍ ከሆነ ባለፉት አስር ዓመታት 25 ሚሊዮን የሕፃናት ጋብቻን መከላከል ተችሏል። \n\nበአሁኑ ወቅት ከ18 ዓመት በታች ከሆናቸው አምስት ልጆች አንዳቸው የሚዳሩ ሲሆን ይህ ቁጥር ከአስር ዓመት በፊት ከአራት ልጆችን አንድ ነበር። \n\nእንደ አለም አቀፉ የሕፃናት ድርጅት ከሆነ የደቡብ ኤስያ ሀገራት የሕፃናት ጋብቻ ቁጥርን በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ ተጠቃሽ ሆነዋል። \n\nበህንድ ይህ ሊሳካ የቻለው የተሻለ ትምህርት በመስጠት እና የሕፃናት ጋብቻ ያለውን ጉዳት በማሳወቅ በተሰራው ሥራ ነው። \n\nኢትዮጵያ የሕፃናት ጋብቻን በአንድ ሶስተኛ መቀነስ ብትችልም ችግሩ በአፍሪካ ሃገራት አሁንም ከፍተኛ ነው። \n\nዩኒሴፍ የጾታ ጉዳይ አማካሪ የሆኑት አንጁ ማልሆርታ እንደሚሉት የሕፃናት ጋብቻ በተለይ ሴቶች ህይወት ላይ ከሚያደርሰው ተጽእኖ አንጻር \"የትኛውም መቀነስ የሚያስደስት ዜና ቢሆን ገና ብዙ ርቀት መጓዝ ይጠበቅብናል።\"\n\n\"ሴቶች በልጅነታቸው እንዲያገቡ ሲገደዱ ወዲያውም ሆነ በቀሪው ህይወታቸው ላይ ችግሮች ይከሰታሉ\" ብለዋል። \n\n\"ትምህርት የመጨረስ ዕድሏ ሲቀንስ፤ በባሏ ጥቃት የማስተናገድ እና በወሊድ ጊዜ ለሚደርሱ ችግሮች የመጋለጥ ዕድሏ ከፍተኛ ይሆናል። ትልቅ ማህበረሰባዊ ችግሮች እና ከትውልድ ወደ ትውልድ ለሚዘልቅ ድህነት የመጋለጥ ዕድሏም ከፍተኛ ነው።\"\n\nእንደሪፖርቱ ከሆነ የሕፃናት ጋብቻ ችግር ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት አካባቢ እየሆነ መጥቷል። \n\nከአስር ዓመታት በፊት ከአምስት የሕፃናት ጋብቻ አንዱ ብቻ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሃገራት የሚመዘገብ ሲሆን ይህ ቁጥር ወደ አንድ ሶስተኛ ከፍ ማለቱን ዩኒሴፍ አስታውቋል። \n\nየዓለም ሃገራት መሪዎች በተባበሩት መንግስታት ዘላቂ የልማት ጎሎች መሠረት የሕፃናት ጋብቻን በአውሮፓዊያኑ 2030 ለማስቀረት ቃል ገብተዋል። \n\nይህን ግብ ለማሳካት ጥረቱን በማጠናከር \"በዚህ መጥፎ ተግባር ምክንያት የልጅነት ጊዜያቸው የሚነጠቅባቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህጻናትን መታደግ ይገባናል\" ሲሉ ማልሆትራ አስታውቀዋል። \n\n ", "passage_id": "7179f51881cb2ac1112692a5028de70a" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- መንግሥት በተያዘው በጀት ዓመት በተለያየ ዘርፎች ለሦስት ሚሊዮን ወጣቶችና ሴቶች የሥራ እድል ለመፍጠር በቂ ዝግጅት ማድረጉን የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ መንግሥት ለ20 ሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ለነደፈው የ10 ዓመት የስትራቴጂ ዕቅድ ትግበራ ከማስተር ፋውንዴሽን የተባለ ዓለም አቀፍ ድርጅት ጋር አዲስ የአጋርነት ስምምነት ይፋ ተደርጓል፡፡ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽነር ዶክተር ኤፍሬም ተክሌ በኢትዮጵያ መንግሥትና በማስተር ፋውንዴሽን በተባለ ዓለም አቀፍ ድርጅት መካከል በራዲሰን ብሉ ሆቴል ትናንት በተከናወነው አዲስ የአጋርነት ስምምነት የይፋ ሥነ ስርዓት ላይ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ለሦስት ሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር በቂ ዝግጅት በማድረግ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ባለፉት ሦስት ወራት\nመነቃቃት ከመፍጠር ጀምሮ\nሥራውን ለመምራትም የተለያዩ\nአካላት ያካተተና በጠቅላይ\nሚኒስትር ዶክተር ዐብይ\nአህመድ የሚመራ የሥራ\nዕድል ፈጠራና ኢንቨስትመንት\nመሪ ኮሚቴ እና\nበምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር\nደመቀ መኮንን የሚመራ\nካውንስል ምክር ቤትም\nተቋቁሟል፡፡ ኮሚሽኑ የፌዴራል\nመንግሥትና ክልሎች እጅና ጓንት ሆነው እንዲሰሩ የማስተባበር ሚናውን በመወጣት ላይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡የሥራ ዕድሎቹ በግብርና፣በአምራች\nኢንዱስትሪ(ማኑፋክቸሪንግ)፣በቱሪዝምና\nኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ላይ\nያተኮሩ መሆናቸውን የጠቆሙት\nዶክተር ኤፍሬም፣የዘመኑ የግብርና\nሥራ ለማከናወን ግብርና\nትልቁን ድርሻ መያዙንም\nጠቁመዋል፡፡በየዘርፎቹ የሚፈጠረው የሥራ\nዘርፍን ጨምሮ እያንዳንዱ\nክልል ሚናውን እንዲወጣ\nየሚያስችል ወጥ የሆነ\nዕቅድ መነደፉንም ገልጸዋል፡፡ሥራውን\nመደገፍ የሚችሉ መንግሥታዊና\nመንግሥታዊ ያልሆኑ አካላትን በማሳተፍ ሀብት የማሰባሰብ ሥራን ለማከናወን እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡በኢትዮጵያና በማስተር ፋውንዴሽን መካከል የተከናወነው አዲስ የአጋርነት ስምምነትም ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ዕድሜያቸው ለሥራ ለደረሰ 20 ሚሊዮን ዜጎች ሥራ ለመፍጠር ለነደፋቸው ስትራቴጂ ዕቅድ ትግበራ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፣ የአጋርነት ስምምነቱ ‹ያንግ አፍሪካ ዎርክስ› በሚል ፕሮጀክት አማካኝነት እንደሚከናወንም አስታውቀዋል፡፡ ለፕሮጀክቱም ሦስት ሚሊዮን ዶላር በጀት መመደቡንና ገንዘቡ የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ በሚሰሩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት አማካኝነት ጥቅም ላይ እንዲውል እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ የማስተርካርድ ፋውንዴሽን ፕሬዚዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሪታ ፎይ በበኩላቸው እንደገለጹት ‹ያንግ አፍሪካ ዎርክስ›ፕሮጀክት ዋና ተግባሩና ተልዕኮው ወጣቱ በሥራ ብቻ ሳይሆን በተለያየ ጉዳይ ላይ ክህሎት እንዲኖረው ማስቻልና ባገኘው ክህሎትም ኑሮውን ቀይሮ የተሻለ ዜጋ እንዲሆን ማድረግ ነው፡፡ ፋውንዴሽኑ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለመስራት የተነሳሳውም ኢትዮጵያ የወጣቶች ሀገር በመሆኗና መንግሥትም ለዜጎቹ ሥራ ለመፍጠር ተነሳሽነቱ ከፍተኛ በመሆኑ ነው፡፡አዲስ ዘመን ጥቅምት 20/2012 ለምለም መንግሥቱ ", "passage_id": "af8183af7cf6675bbac9c7a1b719df45" }, { "passage": "በዓለም አቀፍ ደረጃ ካልተከተቡት 20 ሚሊዮን ህፃናት መካከል 3 ሚሊዮኑ ናይጀሪያ ውስጥ እንደሚገኙ አዲስ የወጣ ሪፖርት ያሳያል።\n\nሁለቱ አፍሪካውያን ሀገሮች ኢትዮጵያና ኮንጎም ከሌሎች በተለየ መልኩ ቁጥራቸው ከፍ ያለ ያልተከተቡ ህፃናት ልጆች ያሉባቸው ሀገራት እንደሆኑ ሪፖርቱ ጨምሮ ያስረዳል። \n\nይህ ሪፖርት የወጣው ዝናብ በማይዘንብበት በበጋ ወቅት ሊከሰቱ የሚችሉ ወረርሽኞች ስጋት በሆኑበት ወቅት ነው። \n\nበናይጀሪያ ከኅዳር እስከ መጋቢት ባለው ወቅት የከፋ የኩፍኝ ወረረሽኝ የሚከሰትበት ጊዜ ነው።\n\nበባለፈው ዓመት ከጥር እስከ መስከረም ባለው ወቅት በሰሜን ምሥራቅ ናይጀሪያ አካባቢ 3 ሺህ ያህል የሚሆኑ በኩፍኝ የተጠረጠሩ ህሙማን እንዳሉ ሪፖርት ተደርጓል።\n\nበዚሁ አካባቢ አሁንም ባሉት ግጭቶች የተነሳ የጤና ተቋማት ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ፤ ሰባት ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎችም የጤና ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል። \n\nይህ ሪፖርት እንደ ዓለም ጤና ድርጅት፣ የተባበሩት መንግሥታት የህፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው በጥምረት ያወጡት ሲሆን፤ ከዚህ በኋላም ከፍተኛ የሆነ ወረርሽኝ ሊከሰት እንደሚችል ጠቁሞ። በሽታው ውስብስብ ለሆኑት የሳንባ ምች፣ ዓይነ-ስውርነት እንዲሁም ለሞት እንደሚዳርግ ይገልፃል።\n\nበዚህ ዓመት መጀመሪያ ለግጭት በተጋለጡ አካባቢዎች ላይ በቆየ የሁለት ሳምንት የክትባት ዘመቻ፤ ዕድሜያቸው ከአስር ወራት እስከ አስር ዓመት የሆኑ አራት ሚሊዮን ልጆች ተከትበዋል። \n\n ", "passage_id": "924d155d85aceb15160fe77152bfaa9e" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡– ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከህዳር ወር 2011ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ በቆየው ሀገር አቀፍ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት እድሜያቸው 14 ዓመት ለሆናቸው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ታዳጊዎች ተደራሽ ማድረጉን አስታወቀ፡፡በሚኒስቴሩ የክትባት መርሃ ግብር ባለሙያ አቶ ጌትነት ባይህ ለጋዜጣው ሪፖርተር እንደገለጹት በህዳር ወር 2011ዓ.ም በተጀመረው ሀገር አቀፍ የመከላከያ ክትባት ዘመቻ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተከናወነ ሲሆን፣ ከትምህርት ገበታ ውጭ የሆኑትን ደግሞ ከሶማሌ ክልል በስተቀር በአካባቢያቸው በሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ክትባት ተሰጥቷል፡፡ የክትባት መርሃ ግብሩም በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነና በሶማሌ ክልልም ክትባቱ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ክትባቱ ከመጀመሩ በፊት መካንነትን እንደሚያስከትልና የወሊድ መከላከያ እንደሆነ በህብረተሰቡ ይነገር የነበረውን የተሳሳተ አመለካከት ለመቀየር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ቀድሞ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የቅስቀሳ ሥራ ማከናወኑን የጠቆሙት አቶ ጌትነት፤ ቅስቀሳው አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ታዳጊዎችን ለመከተብ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ያገዘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ጌትነት ገለጻ፣ እስካሁን በተሰጠው ክትባት ለጉዳት የተዳረገ እንደሌለ፤ መጠነኛ ጊዜያዊ ራስ የመሳት ሁኔታ ቢከሰት የመድኃኒቱ ባህርይ እንደሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡አሁን ክትባቱን የወሰዱት ከስድስት ወር በኋላም በድጋሚ ይከተባሉ፡፡ በሽታውን መከላከል የሚቻለው ሁለቴ ከተከተቡ በኋላ ነው፡፡ መርሃ ግብሩ ከስድስት ወር በኋላ በተመሳሳይ ስለሚከናወን ታዳጊዎቹ መዘንጋት የለባቸውም፡፡በ2011ዓ.ም በሀገሪቷ የተጀመረው የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር በሽታ መከላከያ ክትባት መደበኛ ሆኖ ይቀጥላል፡፡የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር በሽታን ቀድሞ መከላከል እንዲቻልና በሽታው ከተከሰተ በኋላም ዓለም ከፍተኛ ደረጃ የደረሰበትን የህክምና ዘዴ ለመጠቀም እንደ ታይላንድ ተሞከሮ ካላቸው ሀገሮች ባለሙያዎችን በመጋበዝ ለሀኪሞች ሥልጠና በመስጠት የበኩሉን ሚና በመወጣት ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር የአባላት ዘርፍና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ዳንኤል ተስፋይ አስታውቋል፡፡አቶ ዳንኤል በተለይም በመከላከሉ ላይ ትኩረት ቢደረግ የታማሚዎችን ቁጥር ከመቀነስ በተጨማሪ በሽታው ካጋጠመ በኃላ የሚወጣውን ገንዘብና ድካም ለመቀነስ በእጅጉ እንደሚያግዝ አመልክተዋል፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በዓለም ላይ በገዳይነታቸው ከሚታወቁት የካንሰር አይነቶች የሴቶችን የመራቢያ ክፍል የሚያጠቃው የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር በሽታ አንዱ ሲሆን፣ በኢትዮጵያም በሁለተኛ ደረጃ ጉዳት እያስከተለ ነው፡፡በየዓመቱ 4ሺ600ሴቶች በማህፀን በር ጫፍ ካንሰር በሽታ እንደሚያዙና ከነዚህ ውስጥም 3ሺ200ዎቹ ህክምና ሳያገኙ እንደሚሞቱ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 26/2011ለምለም መንግሥቱ", "passage_id": "dfa421107a58a2c4b78b7fb37bdc49b1" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሚቀጥሉት 10 አመታት ለ10 ሚሊየን ወጣቶች የስራ እድል የሚፈጥር ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።ፕሮጀክቱ በዛሬው እለት በኢትዮጵያ የስራ እድል ፈጠራ ኮሚሽን እና በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን አማካኝነት ነው ይፋ የተደረገው።የስራ እድል ፈጠራ ኮሚሽነሩ ዶክተር ኤፍሬም ተክሌ የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ወጣቶችን የስራ ባለቤት ለማድረግ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን በዚህ ወቅት ተናግረዋል።አያይዘውም መንግስት ወጣት እና ሴቶችን የስራ ባለቤት ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ነው የተናገሩት።የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስራ አስፈጻሚ ሪታ ሮይ በበኩላቸው ፋውንዴሽኑ በኢትዮጵያ ያለውን የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ 300 ሚሊየን ዶላር በጀት ተይዞለታል።የአሁኑ ፕሮጀክት ፋውንዴሽኑ በአፍሪካ ከሚያደርገው እንቅስቃሴ ውስጥ 1/3 የሚሸፍን ነው ተብሏል።  በአዳነች አበበ", "passage_id": "d6982f6ac0c2e23c51b61a02999e9328" } ]
1e90d47f2fe241729cdf2e7449f1f701
f7a1137ec576488975808084b5e38675
በዘንድሮ የመስኖ ልማት ከቆላማ አካባቢዎች በተጨማሪ በሌሎች ክልሎች ለማስፋት መታቀዱ ተገለጸ
እፀገነት አክሊሉ ባለፉት ሁለት ዓመታት በቆላማ አካባቢዎች ላይ ስንዴን በመስኖ በማልማት የተገኘውን ውጤት በመቀመር ዘንድሮ ደግሞ ወደሌሎች ክልሎች በማስፋት ውጤታማ ሥራዎችን ለመሥራት መታቀዱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። በግብርና ሚኒስቴር የአነስተኛ መስኖ ልማት ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ አወል በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት ባለፉት ዓመታት በተለይም በቆላማ አካባቢዎች ላይ ስንዴን በመስኖ ለማልማት የተጀመረው ሥራ እንደ ጠቅላላ መልካምና ጥሩ ውጤት የታየበት ነበር፤ በዚህም በአፋርና በሶማሌ ክልሎች ላይ የተሠሩት ሥራዎች ብዙ ጥረት የጠየቁ ቢሆንም በውጤት ደረጃ ግን ሲመዘኑ አበረታች ናቸው።እንደ አቶ ኤልያስ ገለጻ ዘንድሮ ደግሞ ያለፉትን ጊዜያት ተሞክሮ በመቀመርና ከቆላማ አካባቢዎች በተጨማሪ በአማራ። ኦሮሚያና ደቡብ ላይ መስኖን በመጠቀም የተለያዩ ሰብሎችን ለማምረት ታቅዷል። በዚህም መሰረት ክልሎች የየራሳቸውን እቅድ ይዘው እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ አብራርትዋል። በየዓመቱ የመኸሩ የግብርና ሥራ እንደተጠናቀቀ የሚገባው ወደመስኖ ሥራ ነው ያሉት አቶ ኤልያስ ፤ በያዝነው ዓመትም ይህንኑ አቅጣጫ በመከተል ለአመራሩ የግንዛቤ ማስፋት እስከ ወረዳ ድረስ ላሉ ባለሙያዎች ደግሞ ስልጠናዎችን በመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አምና የመስኖ ሥራውን ለማስፋፋት በአብዛኞቹ ክልሎች ላይ ከከርሰ ምድር ውሃን ለመሳብ የሚያገለግሉ የውሃ መሳቢያዎች (ፓምፖች) በየክልሎቹ የማከፋፈል ሥራ ተከናውኗል ያሉት አቶ ኤልያስ፤ አሁን ላይ በብልሽት የቆሙም ካሉ ተጠግነው ሙሉ በሙሉ ወደሥራ እንዲገቡና የግብርና ሥራውን እንዲያቀላጥፉ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። በሌላ በኩልም በግብርና ሚኒስቴር የሚተዳደሩ የመስኖ አውታሮች በተለያዩ ፕሮጀክቶችና በመንግሥት በጀት የሚሠሩ እንዳሉ የገለጹት አቶ ኤልያስ እነዚህም አምና የተጀመሩ በመሆኑ አሁን በተጠናከረ መልኩ ተጠናቀው ወደ ሥራ መግባት ስላለባቸው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል። በተመሳሳይም አርሶ አደሩ በራሱና በቤተሰቦቹ ጉልበት እንዲሁም በአቅራቢያው የሚገኙ ቁሳቁሶችን ተጠቅሞ ከከርሰ ምድር ውሃ እያወጣ እንዲሁም በጓሮው የውሃ ማቆር ሥራን እያከናወነ የልማት ሥራውን እንዲያከናውን ሰፋፊ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይም በቤተሰብ ደረጃ የተዘጋጁትን ከጥር ወር ጀምሮ ወደሥራ ለማስገባትና ውጤታማ ሥራን ለማከናወን እንደ ግብርና ሚኒስቴር ዝግጅቱ መጠናቀቁንም አብራርተዋል።የዘንድሮው የመስኖ ሥራ ከወትሮው በተለየ መልክ አምበጣም ኮሮና ቫይረስም በምርት ላይ ያሳደሩትን መጠነኛ ተጽዕኖ ለማለፍ በሚያስችል መልኩ ለመሥራትና ውጤታማ ለመሆን የሚያስችል ዝግጅት ስለመኖሩም ጠቁመዋል። በዚህ መሰረት በዘንድሮው የመስኖ ልማት ሥራ በሽፋንም በአጠቃላይ በምርትም በኩል ጥሩና አበረታች ለውጦች ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኤልያስ ተናግረዋል። በተለይም በስምጥ ሸለቆ አካባቢ ባሉ ቦታዎች ላይ እንደ ሽንኩርት߹ ቲማቲምና ቃሪያ የመሳሰሉ አትክልቶችን በማምረትና ወደገበያ በማምጣት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታ የመስኖ ውሃ መሳቢያ ማሽኖች (ፓምፖች) መሰራጨታቸውንና ይህ ሥራ ደግሞ በግለሰብ ደረጃም እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተደራጅተው የሚሠሩት መሆኑን ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37620
[ { "passage": "አምቦ፡- የግብርና ሥራን ለማዘመን ተስፋ የተጣለበት የላይኛው ጉደር የመስኖ ፕሮጀክት በጉደርና ጥቁር እንጭኒ አካባቢ ተጀመረ። ፕሮጀክቱን ለማስጀመር ትናንት በስፍራው ተገኝተው የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጡት የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደተናገሩት፤ ፕሮጀክቱ 3ነጥብ4 ቢሊዮን ብር በጀት እንደተያዘለት ገልፀዋል።ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ 4ሺ926 ሔክታር መሬት የማልማት አቅም ያለው ሲሆን ከ10ሺ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል። በምዕራብ ሸዋ ዞን ቶኬ ኩታዬ ወረዳ በሚገኘው ፋጦ ወንዝ ላይ የሚገነባው ግድብ ከመስኖ ፕሮጀክቱ ባሻገር የአካባቢውን የንፁህ ውሃ አቅርቦት ችግር እንደሚያቃልል የገለፁት ሚኒስትሩ፣ የግብርና ስራዎችን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ አርሶ አደሩን በዓመት ሦስት ጊዜ ለማምረት እንደሚረዳው ተናግረዋል።የላይኛው ጉደር መስኖ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ፤ ከአርባ ሜትር በላይ ጥልቀት፣ ከ273 ሜትር በላይ ስፋትና 57ነጥብ 7 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ይይዛል ብለዋል፡፡ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በመርሐግብሩ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ የፌዴራል እና የክልሉ መንግስት የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ መካከለኛና አነስተኛ ግድቦችን በተለያዩ አካባቢዎች ለመገንባት ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል።የላይኛው ጉደር የመስኖ ፕሮጀክትም ከግብርና በተጨማሪ ለአሳ እርባታና ለቱሪዝም ምቹ በመሆኑ ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር እንደሚችል ተናግረዋል።የአካባቢው ህብረተሰብም የግድቡ ግንባታ እንዲፋጠን የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል። ግንባታውን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እንዲሁም የኦሮሚያ ውሃ ስራዎች ያከናውኑታል።በሦስት ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅም ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 1/2011", "passage_id": "ef9fc902f281f35a0af1363b1ccc799a" }, { "passage": "በፌደራል ደረጃ ከሚከናወኑ የግድብና የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል የጊዳቦ ግድብ፣ የመገጭ ሰርባና የርብ የመስኖ መሬትዝግጅት ፕሮጀክቶች ሥራ ተጠናቀው በዘንድሮ የበጀት ዓመት አገልገሎት  መሥጠት እንደሚጀምሩ የውሃ ፣መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር  አስታወቀ ። የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋሚኮ  እንደገለጹት በመላ አገሪቱ  በፌደራል  ደረጃ  እየተከናወኑ  ካሉት  ሰባት  የግድብና  የመስኖ ዝግጅት ፕሮጀክቶች መካከል የጊዳቦ ግድብ ፣ የመገጭ ሰርባ የፓንፕ መስኖና የርብ የመስኖ መሬት  ዝግጅት በዘንድሮ የበጀት  ዓመት ለማጠናቀቅ  እየተሠራ ይገኛል ።እንደ አቶ ብዙነህ  ገለጻ  እስካሁን ድረስ በተካሄደው  የግንባታ ሥራ  የጊዳቦ ግድብ ፕሮጀክት አፈጻጻም  96 ነጥብ  66 በመቶ ፣ የመገጭ ሰርባ  የፓንፕ መስኖ ግንባታ ሥራ  ፕሮጀክት  93 ነጥብ 65  በመቶና የርብ  የመስኖ መሬት ዝግጅት 55 ነጥብ 62 በመቶ ሥራው በመጠናቀቁ በዘንድሮ ዓመት አገልግሎት መሥጠት ይጀምራሉ ተብሎ በዕቅድ ተዟል ብለዋል  ።ግንባታቸው በመከናወን ላይ የሚገኙት የመገጭ ግድብ 46 በመቶ ፣ አርጆ ደዴሳ 49 ነጥብ 72 ፣ ዛሬማ ሜይዴይ 82 ነጥብ 28 በመቶና  ሥራቸው መጠናቀቁን የጠቆሙት አቶ ብዙነህ የወይጦ ግድብ ጥናትና ዲዛይን 83 በመቶ  እንዲሁም የአንገር መስኖ ልማት  ዝርዝር ጥናትና ዲዛይን 90 ነጥብ 6 ሥራው ተገባዷል  ።የውሃ ፣ መስኖና  ኤሌክትሪክ  ሚኒስቴር በፌደራል ደረጃ የተያዙ የግድብና የመስኖ ፕሮጀክት ሥራዎች  በተያዘላቸው  የጊዜ  ገደብ መሠረት  እንዲጠናቀቁ  ለማድረግም  ጥብቅ  ቁጥጥር፣ ክትትልና  ድጋፍ እያደረገ ስለመሆኑ አቶ ብዙነህ ተናግረዋል ።ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በዘንድሮ የበጀት ዓመት በፌደራል ደረጃ አዲስ  የመስኖና ግድብ  ፕሮጀክት እንደማይጀመርና  የተጀመሩ  ፕሮጀክቶችን  በማጠናናቅ ላይ ትኩረት ተሠጥቶ እንደሚሠራ  አቶ ብዙነህ አመልክተዋል ።በመላ አገሪቱ  በግንባታ  የሚገኙ  የመስኖና የግድብ  ፕሮጀክቶች  ሙሉ ለሙሉ  ተጠናቀው    ለህብረተሰቡ አገልገሎት  መሥጠት ሲጀምሩ  በአጠቃላይ  210ሺህ ሄክታር  መሬት  በማልማት   ከ 153 ሺህ በላይ  አርሶአደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ መሆኑን ከውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር  የወጣው መረጃ  ጠቁሟል", "passage_id": "0104900aedec9203f350db588bb25d6f" }, { "passage": "ደሎ መና:- በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ ውስጥ በሦስት ቢሊዮን ብር ወጪ 11 ሺ 40 ሄክታር መሬት የሚያለማ የወልመል መስኖ ልማት ሥራ በይፋ ተጀመረ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለና የፌዴራል የመስኖ ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ሚካኤል መሃሪ ትናንት በስፍራው ተገኝተው የፕሮጀክቱን ሥራ በይፋ አስጀምረዋል። የፌዴራል የመስኖ ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ሚካኤል መሃሪ ፕሮጀክቱ ይፋ በተደረገበት ወቅት እንደገለጹት፤ በፌዴራል መንግሥት ከታቀዱት ሁለት የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል 11 ሺ 40 ሄክታር መሬት ላይ የሚያለማው የወልመል ፕሮጀክት የወልመል ወንዝን በመጥለፍ የሚለማ ሲሆን፤ 22 ሺ አባወራ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል። ሁለተኛው ደግሞ በአራት ሺ 600 ሄክታር ላይ የሚለማውና ከሮቤ 170 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የጨልጨል ፕሮጀክት ነው። ቆላማና የመልማት አቅም ባላቸው አካባቢዎች ሰፊ የመስኖ ልማት ዝርጋታዎችን የማከናወን ሥራ በመንግሥት ታቅዶ እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ሚካኤል፤ እነዚህ ፕሮጀክቶች ከዚህ ቀደም ከነበሩት የተለየ ባህሪ ያላቸው፣ አገራዊ ለውጥ የሚያመጡና የተፋጠነ የመስኖ ልማትን ለማከናወን የሚያስችሉ መሆናቸውን አስረድተዋል።የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው፤ በክልሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ይህ አሁን ይፋ የሆነውን ጨምሮ ለአገልግሎት የበቁት ፕሮጀክቶች ትልቅ የልማት አቅም እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል። አቶ ሽመልስ ፕሮጀክቶቹ ዝናብ ጠብቆ ከማልማት ለመላቀቅ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዙ ገልጸው፤ በዚህ ረገድ የፌዴራል መንግሥት ክልሉ ለሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ምርትን ወደ ገበያ ለማውጣት እንደ መንገድ ያሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች ጎን ለጎን እንደሚከናወኑም ተናግረዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በበኩላቸው፤ ድህነትን ታሪክ ለማድረግ እና አንቱ የተባሉ የክልሉን ጀግኖች ስም ለማስጠራት እንዲህ ያሉ የልማት ስራዎች ወሳኝ በመሆናቸው በከፍተኛ ርብርብ ማከናወን ከህዝቡ በተለይም ከወጣቶች እንደሚጠበቅ አሳስበዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ሁሉም ወደ ልማት ፊቱን እንዲያዞር እና አካባቢውን እና አገሩን በጋራ እንዲያለማ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፤ የኦሮሚያ ክልል ህዝብ በልማት፣ በአብሮነት፣ በፍቅርና በመተሳሰብ የሚታወቅ እንደሆነም ገልጸዋል። ዶክተር ዐብይ መደመር፣ አብሮነት፣ ፍቅርና መተሳሰብ አንዱ ለሌላው ማሰብን፣ በጋራ ማልማትን የሚያመለክት መሆኑን ገልጸዋል። ይፋ የሆነው ፕሮጀክት በፌዴራል መንግሥት በጀት የሚሸፈን ሲሆን በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል። የፕሮጀክት ስራውን እንዲያከናውኑም የኦሮሚያ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝና አለማየሁ ከተማ ጄነራል ኮንስትራክሽን ለተባሉ ድርጅቶች መሰጠቱ ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን ጥር 27/2012ለምለም መንግስቱ", "passage_id": "b540b8e0f9903b0809ab6ee9c69d473a" }, { "passage": "ለግብርናው ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረት ተከትሎ ምርትና ምርታማነት በየአመቱ እያደገ ነው፡፡ የአርሶ\nአደሩም ሕይወት በዚሁ ልክ እየተለወጠ ይገኛል፡፡ ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተው አስተዋጽኦም አሁንም ከፍተኛ ነው፡፡ ከአጠቃላይ\nየሀገር ውስጥ ምርት ውስጥ ኢንዱስትሪው በተለይ የአገልግሎት ዘርፉ ጉልህ ስፍራ እየያዙ ቢመጡም ግብርናው 40 በመቶውን  እየሸፈነ ነው፡፡ይሁንና ግብርናው በሚጠበቅበት ልክ እየተጓዘ ነው ወይ የሚለው ጥያቄ ሲነሳ ፣ መልሱ አይደለም የሚል\nነው፡፡  ችግሩ አንድም ከዘርፉ አለመዘመን ጋር ይያያዛል፡፡ ሀገራችን\nዛሬም በእንስሳት ጫንቃ ላይ ተመስርታ ነው ግብርናዋን እያካሄደች የምትገኘው፡፡ ባለሀብቶች ዘርፉን እንዲቀላቀሉ ቢሰራም የተፈለገውን\nለውጥ ማምጣት አልተቻለም፡፡ ግብርና የሚጠበቅበትን እየተወጣ ላለመሆኑ ስንዴ በቢሊዮን ዶላሮች እየወጣ የሚገባዘበት ሁኔታ ያመለክታል፡፡\nሀገሪቱ ስንዴ ለማምረት የሚያስችል መሬትም ስነ ምዳርም እያላት ነው ለተለያዩ የልማት ስራዎች ከሚያስፈልጋት ላይ የውጭ ምንዛሬ\nእያወጣች ስንዴ የምትገዛው፡፡የግብርናው አለመዘመን ግንባታቸው እየተካሄደ ለሚገኘው የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪዎችም ስጋት\nነው፡፡ ኢንዱስትሪዎቹ የግብርና ምርትን በግብአትነት የሚጠቀሙ እንደመሆናቸው ይህ ግብአት በሚፈለገው መልኩ ካልተገኘ ከኢንዱስትሪዎች\nየሚጠበቀውን ማሳካት ያዳግታል፡፡ይህ ሁሉ ግብርናውን ይበልጥ የማዘመን አስፈላጊነትን ያስገነዝባል፡፡ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር\nዶክተር አብይ አህመድም የግብርናውን መዘመን አስፈላጊነት በተደጋጋሚ አስገንዝበዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለይ በመስኖ እርሻ ላይ\nበትኩረት የመስራት አስፈላጊነትን የሀገሪቱን የውሃ  ሀብት በመጠቀም\nበረሃዎቻችን ገነት ማድረግ አለብን ብለዋል፡፡ የሚቀጥለው በጀት አመትም በመስኖ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡በእርግጥም የግብርናውን ምርታማነት ለማረጋገጥ የመስኖ ልማት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል፡፡\nእስከ አሁን በተከናወኑ ተግባሮች በአነስተኛ መስኖ አርሶ አደሩ በዓመት አንዴ ከሚያመርትበት ሁኔታ ወደ ሁለት እና ሶስቴ ማድረስ\nእየተቻለ ነው፡፡ይህ የመስኖ ልማት ግን ከአትክልት እና የተወሰኑ ሰብሎች ልማት ያለፈ አይደለም፡፡ ሀገሪቱ ኢኮኖሚዋ\nየሚጠይቀው የግብርና ምርት ከፍተኛ እየሆነ እንደ መሆኑ ሰፊ የግብርና ልማት ስራ ውስጥ መግባት ይኖርባታል፡፡ ለእዚህ ደግሞ መስኖ\nትልቅ አቅም አለው፡፡በኢትዮጵያ ከ3 ነጥብ 7 እስከ 4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር በመስኖ ሊለማ የሚችል መሬት አለ፡፡\nከዚህ ውስጥ በመስኖ እየለማ ያለው ግን 7 እስከ 10 በመቶው ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን ይህን ሰፊ መሬት ማልማት የሚችል የገጸ ምድርና\nየከርሰ ምድር ውሃ አለ፡፡ ስለሆነም ይህን እምቅ አቅም አውጥቶ መጠቀም ወሳኝ ነው፡፡ መንግስት ይህን አቅም ለመጠቀም ፍኖተ ካርታ\nእያዘጋጀ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት በሰው ሀብት፣በፋይናንስ፣በቴክኖሎጂ እና በአደረጃጀት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችም ተለይተዋል፡፡ፍኖተ ካርታው የመስኖ እርሻ አስፈላጊ ነው ብሎ ብቻ የእስከ አሁኖቹን መለስተኛ የመስኖ ስራዎች\nተሞክሮ ብቻ ይዞ ወደ ልማቱ ዘሎ ከመግባት ያድናል፡፡ በፍኖተ ካርታው ላይ በመመስረትም ቀጣይ ስራዎችን ማከናወን  ይገባል፡፡አሁን የሚያስፈልገው ወደ ልማቱ በቀጥታ መግባት ብቻ ይሆናል፡፡ መንግስት የመስኖ ልማቱን አስፈላጊነት\nበፍኖተ ካርታውም አረጋግጧል፡፡ ስራው ግን ከዚህም በላይ ያለፈ መሆን ይኖርበታል፡፡ ስራውን መሬት ላይ ለማውረድም ቁርጠኝነቱን\nማረጋገጥ ይጠበቅበታል፡፡ ስራው በእርግጥም ግዙፍ ነው፡፡ በኢንዱስትሪ ልማቱ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን  ፣ የሃይል ማመንጫዎችን ፣የስኳር ፋብሪካዎችን ወዘተ ለመገንባት የተወሰደውን\nቁርጠኝነት በመስኖ ልማቱም መድገም ያስፈልጋል፡፡ለመስኖ ልማት የሚወጣ ሀብት በትክክል ከተሰራበት አትራፊ እንደሚሆን የዘርፉ ባለሙያዎች ይጠቁማሉ፡፡\nልማቱ በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ በተለይ በሰፋፊ የመስኖ ልማት ስራዎች ላይ ማተኮር ይገባል፡፡እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ ነው፤ ኢኮኖሚው በኢንዱስትሪው እንዲመራ ይጠበቃል\n፤ የኢንዱስትሪዎች ግብአት እንዲሆን የሚጠበቀው  ደግሞ የግብርና ምርት\nነው፡፡ ለልማታችን የምንፈልገውን የውጭ ምንዛሬ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ መሰረት ማስገኘት  የሚችለውም ግብርናው ነው፡፡እነዚህ እውነታዎች የግብርናውን መዘመን በእጅጉ ይፈልጋሉ፡፡ መዘመኛው  አንዱ መንገድ በዓመት ከአንድ ጊዜ በላይ ማምረት የሚያስችለው የመስኖ እርሻ\nእንደመሆኑ መስኖን የልማቱ መዘወሪያ ማድረግ ይገባል፡፡     ህዝቡን በበቂ ሁኔታ መመገብ፣ የኢንዲስትሪዎችን ግብአት ማሟላት ፣ ለቀጣይ ልማት የሚያስፈልገውን\nየውጭ ምንዛሬን ማስገኘት የሚቻለው ግብርናውን በማዘመን ነው፡፡ ይህን ሁሉ ታሳቢ ያደረገ ዘመናዊ ግብርና ለማካሄድ ሲታሰብ ብዙም\nበአጠገቡ ያልዞርንበትን ከፍተኛ እምቅ እቅም ያለውን የመስኖ ልማት ለመጠቀም የመንግስት ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው፡፡አዲስ ዘመን የካቲት 19/2011", "passage_id": "1e8d5f9081208b0a71d6d6790613b4bf" }, { "passage": "የኦሮሚያ ክልል በሁለተኛ ዙር 670ሺ ሄክታር መሬት በመስኖ ለማልማት ዝግጅቶችን እያጠናቀቀ መሆኑን  የኦሮሚያ መስኖ  ልማት ባለሥልጣን  አስታወቀ ።የባለሥልጣኑ ዋና ኃላፊ አቶ ሰይፈዲን መሓዲ ለዋልታ እንደገለጹት በኦሮሚያ ክልል በሁለተኛ   ዙር በትናንሽ ፣ በመካከለኛና በትላልቅ የመስኖ ሥራዎች 670ሺ  ሄክታር መሬት ለማልማት እየተዘጋጀ ነው ። በክልሉ በመጀመሪያ ዙር 1ነጥብ3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ ለማልማት ታቅዶ 86 በመቶ ወይም  977ሺ ሄክታር መሬት እንዲለማ ተደርጓል ያሉት አቶ ሰይፈዲን  በመስኖ ሥራው 1ነጥብ 7 ሚሊዮን አርሶአደሮች ተሳትፈዋል ።እንደ አቶ ሳይፈዲን ገለጻ በክልሉ የሚካሄደውን የመስኖ ልማት ስኬታማ ለማድረግ  1ሺ 620 ለሚሆኑ የግብርናና የልማት ባለሙያዎች የአሠልጣኞች ሥልጠና በዘንድሮ የበጀት ዓመት  ተሠጥቷል ።ለግብርናና የልማት ባለሙያዎች የተሠጠው ሥልጠና በመስኖ ልማት ቴክኖሎጂ፣ በውሃ ቁጠባ አሠራርና የግብይት  አጠቃቀም  ላይ የሚያተኩር  መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሰይፈዲን  ሠልጣኞቹ በሥልጠና ያገኙትን ተሞክሮ በክልሉ የሚገኙ አርሶአደሮች እያስተላላፉ ይገኛሉ ብለዋል ።በአሮሚያ ክልል  በተለያዩ ደረጃዎች 2ነጥብ 45 ሚሊዮን  የሚሆኑ አርሶአደሮችና ከፊል አርሶ አደሮች በየዓመቱ  በመስኖ ሥራ እየተሳተፉ እንደሚገኙና  የክልሉ መንግሥትም  ለመስኖ ሥራዎች ማስፈጸሚያ  470 ሚሊዮን ብር መመደቡን አቶ ሰይፈዲን አያይዘው ገልጸዋል ።በኦሮሚያ ክልል 533 የሚሆኑ የመስኖ አውታሮች የሚገኙ  ሲሆን   የመስኖ  አውታሮችን ይበልጥ ለማስፋፋት  የክልሉ መንግሥት ጥረት እያደረገ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል ።     ", "passage_id": "92344ba5f0918a1099534338c7fc618b" } ]
f5393d3ace043dcdbd271143d40c3339
2927a11a70c050d67c4269e9273f9a26
የጋራ ሀብት ለጋራ ጥቅም
ጽጌረዳ ጫንያለው የህወሓት ጁንታ የአገሪቱን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በጥቂት ተቋማቱ አማካኝነት የግሉ አድርጎት ቆይቷል። ነገር ግን ሲጠቀምበት የቆየው የአገር ሀብት በመሆኑ እነዚህ የታገዱ ተቋማት በመንግሥት ተወርሰው አገርን ተጠቃሚ በሚያደርጉበት መልኩ ሊሠራባቸው እንደሚገባ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይናገራሉ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚ መምህር ዶክተር አሰፋ አድማሴ እንደተናገሩት፤ ነፃ ገበያ ማለት ዋና መርሁ ሁሉም በእኩል ደረጃ መገበያየት የሚለውን ይይዛል። የማወዳደሪያ ሜዳውም እኩል የሆነ ነው። ነገር ግን የህወሓት ጁንታ የሃገሪቱን ሀብት በመዝረፍ በቁጥጥሩ ስር አድርጎ በመቆየቱ፤ ገበያውን እኩል መቀላቀል አይፈቀድም ነበር። በዚህም ያለፉት በርካታ ዓመታት እንደ አገር የነበረው ኢኮኖሚ በጥቂቶች የተያዘና ጥቂቶች የሚዘውሩት ነበር። በተለይም ከመንግሥት ጋር የተጣበቁ ኩባንያዎች፣ ድርጅቶችና ግለሰቦች የበላይነትን ያገኙበት ነበር። የመወዳደሪያ መንገዱንም ለሥርዓቱና ለራሱ ተከታዮች ብቻ በማድረግ ሜዳውን አጥብቦት ቆይቷል። ይህ ደግሞ ሀቀኛ የነበሩ ግለሰቦች፣ ድርጅቶችና ኩባንያዎችን ከጨዋታ ውጪ አድርጓቸዋል። እንደ ዶክተር አሰፋ ማብራሪያ፤ አሁን ታገዱ የተባሉት የጁንታው ኩባንያዎች በተለይ የአገሪቱን ማክሮ ኢኮኖሚ ሲዘውሩት ነበር። በነፃ ገበያ ስም ከሥርዓቱ ጋር እጅና ጓንት የነበሩ የተጠቀሙበት ነው። በዚህም ህግ የሚያስፈጽሙ ህጋዊ ተቋማት ሳይቀሩ የዚህ ድርጊት ተሳታፊ ነበሩ። ስርዓቱን ለማስፈጽም የተለያዩ ቢሮክራሲ ተጠቅመው የአገር ሀብትን እንዲበዘበዝ አድርገዋል። ህጋዊ የሆኑ ኩባንያዎች፣ ድርጅቶችና ግለሰቦችም ከጨዋታ ውጪ እንዲሆኑ በማድረግ የአገር ሀብት ወደ አንድ ቋት እንዲገባም ሲሠሩ ነበር። የኢኮኖሚ ጉዳይ የህወሓት ጁንታ መወገድ ጉዳይ ብቻ እንዳልሆነ የሚያነሱት ዶክተር አሰፋ፤ ስርዓቱ ሙሉ ለሙሉ ካልተወገደና አሠራሩ በሚባለው የኢኮኖሚ ህግ መመራት ካልቻለ አሁንም ቢሆን ችግሩ አይቀሬ ነው፤ የህወሓት ጁንታ የፈጠረው አስተሳሰብ አሁንም በኢኮኖሚው ሴክተር ላይ ይታያል ብለዋል። እነዚህ የጁንታው የንግድ ተቋማትም አሁን መታገዳቸው እንዳለ ሆኖ ወደ ተግባር ሲገቡም ጥንቃቄ እንደሚያስፈልጋቸው ጠቁመዋል። የኢኮኖሚና ፖለቲካ ምሁሩ አቶ ሸዋፈራሁ ሽታሁን በበኩላቸው እንደሚናገሩት፤ እንዲህ ዓይነት ችግሮች የሚፈጠሩት የአገሪቱ ልሂቃን የአገሪቱን አንጡራ ሀብት ለታችኛው የህብረተሰብ ክፍል የሚደርስበትን ሁኔታ የሚወስኑበት ተቋማዊ አሠራር ሲጠቀሙ ነው። ይህም ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ይባላል። ስለሆነም የህወሓት ጁንታም የተጠቀመው ይህንን አሠራር ነው። በዚህም እርሱ ለፈቀዳቸውና አጋሬ ናቸው ለሚላቸው ገበያውን አመቻችቷል። ተጠቃሚም አድርጎበታል። ይህ ደግሞ ጥቂቶች በአገሪቱ ሀብት እንዲያዙ ዕድል ሰጥቷቸዋል። የፖለቲካ ስልጣን የያዘ አካል ሀብቱን የመያዝ ዕድሉ የተመቻቸ በመሆኑ ኢኮኖሚውን መዘወሩ እንደማይቀር የሚገልጹት አቶ ሸዋፈራሁ፤ የህወሓት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ስርዓትን ተከታይ እንደመሆኑ ይህ አስተሳሰብ ጠላትና ወዳጅን የመያዝን መርህ የተከተለ እንደሆነ አስረድተዋል። በመሆኑም ልማታዊ ባለሀብት፣ አርሶአደር፣ ወዘተ፣ እያለ ከእርሱ ወገን ያሰለፈውን ሲጠቅም የቀድሞ ናፋቂ ያላቸውን ደግሞ ሲጎዳና ከውድድር ውጪ ሲያደርግ መቆየቱን ተልጸዋል። በዚህ አስተሳሰቡም የአገሪቱን ሀብት የጥቂቶች መፈንጫ ማድረጉን እና ዛሬ ታገዱ የተባሉት ተቋማትም የተፈጠሩት በዚህ አማካኝነት እንደሆነ ይናገራሉ። የህወሓት ጁንታ ደግሞ ለሞራልም ለህግም የማይገዛ በመሆኑ ነው የአገሪቱን ሀብት በጥቂቶች እጅ እንዲገባ ያደረገው የሚሉት የምጣኔ ሀብት ባለሙያው፤ በራሱ ብቻ የሚንቀሳቀስ ባለመሆኑ በአጋሮቹ አማካኝነት ጭምር ተቋማትን መስርቶ ታክስ የማይከፍሉ፣ ብድር ወስደው የማይመልሱ አድርጓል። ከዚያም አልፎ የአገሪቱ ሀብት ወደ አገር እንዳይመለስ እንዲባክንና ወደውጪ እንዲወጣ በታትኖታል። ሀገሪቷንም እዳ አሸክሟታል። ከዚያ ያለፈውን ደግሞ በብሔር እየከፋፈለም ሀብቱ በታገዱት ተቋማት አማካኝነት እንዲቀመጥ እንዳደረገም ይገልጻሉ። መፍትሔው የህወሓትን ጁንታ ሲደግፉና በሞኖፖል የአገሪቱን ገበያ ሲይዙ የነበሩ ተቋማት መታገዳቸው አንዱ መሆኑን የሚጠቁሙት ዶክተር አሰፋ፤ የተቋማቱ መታገድ የገበያ ተወዳዳሪነታቸውን ያሳልጣል፤ የእውነተኛ ተቋማትን ተወዳዳሪነትን አብዝቶ ነጋዴውም ሆነ ሸማቹ በእኩል ደረጃ እንዲጠቀም ያስችላል። አገር ላይ እየታየ ያለው የዋጋ ግሽበት ተጽዕኖም ይቀንሳል። ዋጋ የሚተመነው ሜዳ ላይ በሚደረገው ፉክክርና ባለው አገልግሎት ልክ ይሆናል። በተለይ እስከአሁን ቅሬታ የነበረው የመወዳደርና ገበያውን የመቀላቀል ጉዳይን መፍትሔ ይሰጣል፤ ሲሉ አብራርተዋል። እነዚህ ተቋማት በመታገዳቸው ጊዜያዊ የሆኑ ችግሮች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ የሚያነሱት ዶክተር አሰፋ፤ እስከአሁን በነበረው ሥርዓት ገበያውን ጠቅልለው የያዙት ጥቂቶች በመሆናቸው ሌሎች ተወዳዳሪ ግለሰብና ድርጅቶች እንዳይኖሩ ሆናል። ስለዚህም የተወዳዳሪ ድርጅቶች እጥረት ያጋጥማል። ነገር ግን ፍላጎትን በማስፋትና ውድድሮችን ክፍት በማድረግ በአሠራር ይህንን መመለስ እንደሚቻል አስረድተዋል። አቶ ሸዋፈራሁ በበኩላቸው፤ መፍትሔ ነው የሚሉትን ያነሳሉ። የመጀመሪያው የታገዱ ተቋማት በመንግሥት መወረስ አለባቸው። ወደ ግል ተዛውረው ቁጥጥሩ በመንግሥት ሆኖ አገራዊ ዓላማን አንግበው አገልግሎት መስጠት ይኖርባቸዋልም ባይ ናቸው። ምክንያታቸውም ተቋማቱ ከአመሰራረታቸው ጀምሮ የአገር ሀብት የፈሰሰባቸው ናቸው። የባለቤትነት ጉዳይም ሌላው ችግር ይሆናል። ተቋማቱ የተቋቋሙት በኢትዮጵያ ሀብት በመሆኑ የኢትዮጵያውያን እንጂ የአንድ ብሔር አይደሉም። ስለሆነም የባለቤትነት ጥያቄን እንዳያስነሱ ተደርጎ ሊሠራባቸው ይገባል። እነዚህ ተቋማት በኢኮኖሚው ህግ መሪ ሴክተር ሞዴል ሊሆኑም የሚችሉ ናቸውና አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን እንዲመሩና ተጠቃሚነቱ የአገር እንዲሆን ማድረግ ከተቻለ እስከ ዛሬ የነበሩትን ስህተቶች በማረም ጭምር ዕድል እየሰጡ ያስጉዙናል ይላሉ። በተደረጉ አንዳንድ ውሳኔዎች ብቻ ለውጡ ከመጣ በኋላ ከፋይናንስ ተቋማት ውስጥ በዋናነት የሚጠቀሱት ባንኮችና ኢንሹራንሶች ከፍተኛ ለውጥ አምጥተዋል። ለአብነት አሥራ ስድስቱ የግል ባንኮች ያስመዘገቡት ትርፍ ከአሥር ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል። ከ120 ሚሊዮን ብር ጀምሮ እስከ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር አትርፈዋል። የባንኮቹ ተቀማጭ ገንዘብም ቢሆን እንዲሁ ከ720 ቢሊዮን ብር በላይ ሆኗል። አጠቃላይ ሀብታቸውም ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ እንደደረሰ የ2010 ሪፖርት ያስረዳል። የኢንሹራንስ ኩባንያዎችም እንዲሁ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ያተረፉበትና በጠቅላላው የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ የሰበሰቡበት ዓመት እንደነበር የኢንዱስትሪው ዓመታዊ የሒሳብ ሪፖርት ያመለክታል። በቀጣይ ሁለቱም ባለሙያዎች እነዚህ ተግባራት ቢፈጸሙ የሃገር ሀብት የግለሰቦች መጠቀሚያ አይሆንም ይላሉ። የመጀመሪያው የዴሞክራሲ ስርዓቱን በይበልጥ በህብረተሰቡ ውስጥ ማስረጽ፤ ያለፈው ስርዓት ብዙ ያስተማረው ነገር አለና ያንን ላለመድገም መሞከር፤ ሁሉም የኢኮኖሚ አጋር በእኩል ዓይን እንዲታይ ማድረግ፤ የገበያ ሁኔታን ክፍት ማድረግ ናቸው። አንዱ ተሸናፊ ሌላው አሸናፊ የሚለውን አስተሳሰብም ማስወገድ፤ አሸናፊ ሆኜ እወጣለሁ የሚለውን አስተሳሰብ መስበር፤ ፍትሐዊ የሆነ የምርት ስርዓት፣ የሀብት አጠቃቀምና የኢኮኖሚ ፖሊሲ ማውጣትና ተግባራዊ ማድረግ ሌላው አማራጭ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37634
[ { "passage": "በዚህም መሰረት ለዓመታት ‹በግል ባለሀብቶች እጅ ሊገቡ አይገባም› በሚል መንግስት ሲሟገትላቸው የባጁትን ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫዎች እና የባህር እና ሎጂስቲክ ባለስልጣንን በሙሉ ወይንም ‹በከፊል በአክሲዮን ሽያጭ ወደ ግል ዘርፍ እንዲተላለፉ› ወስኗል፤ይሄ ውሳኔ ከተሰማ በኃላ የድጋፍ እና ነቀፌታ ሀሳቦች ተከትለዋል፡፡\n\nቢቢሲ ባናገራቸው የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ዘንድም ጉዳዩ ለየቅል የሆነ አቀባባል እንዳለው ለማጤን ችሏል፡፡ በመንግስት እጅ ውስጥ የቆዩ የንግድ ድርጅቶችን ወደ ግል የማዞር ጽንሰ ሀሳብ በፖሊሲ ደረጃ ከተያዘ ሃያ ዓመታት ግድም እንዳለፉት የሚጠቅሱት የአግሮ ኢኮኖሚ ባለሙያው ዶ/ር ደምስ ጫንያለው፣ የአሁኑ የመንግሥት እርምጃ ልዩ የሆነው ግዙፍ የንግድ ተቋማት ለግል ባለሀብቶች ተሳትፎ ክፍት ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ እንደሆነ ያስገነዝባሉ።\n\n‹‹ለኢትዮጵያዊያን ባለሃብቶች ክፍት መደረጋቸው ትልቅ እመርታ ነው፡፡ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች (እንደ ኢትዮቴሌኮም) ባሉ ድርጅቶች ውስጥ ገብተው ከፍተኛውን የሀብት ድርሻ ኢትዮጵያዊያን እንዲይዙት ማድረግ ቢቻል ትልቅ ለውጥ ነው›› የሚሉት ዶ/ር ደምስ ውሳኔው የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች እንዲጠናከሩ እገዛ እንደሚያደርግ ያስረዳሉ፡፡ ብዙ ባለሀብቶቻችን ይሄን መሳይ ‹የኢንቨስትመንት› አማራጭ ስላልነበራቸው የባንክ ሼርን መግዛትን በመሰሉ የንግድ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተጠምደው እንደነበርም ያስታውሳሉ፡፡\n\nየቀድሞው የኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት ሃላፊ እና በአሁኑ ጊዜ ‹ኢንሺየቲቭ› አፍሪካ የተሰኘው ተቋም መስራች እና ሾል አስፈጻሚ አቶ ክብር ገና ግን ፈላጊ ያላቸው፣ ትርፍ እያስገኙ ያሉ ትልልቅ የንግድ ድርጅቶችን ለግል ባለሀብቶች ማስተላላፍ ትልቅ ጉዳት እንዳለው ይሟገታሉ፡፡ ለአብነት የሚጠቅሱት ጉዳት ደግሞ፣ ለልማት ስራዎች ማስፈጸሚያ ይውል የነበረው የንግድ ድርጅቶቹ ገቢ ለባለሀብቶች ግላዊ ብልጽግና ብቻ ሊውል የመቻሉን ዕድል ነው፡፡\n\n‹‹ለምሳሌ ኮሚዩኒኬሽን እስከ 2 ቢሊየን ብር ድረስ የዘጠኝ ወር ገቢ ነበረው፡፡ በየዓመቱ እያደገ ያለና ለልማት የሚውል ገቢ ያለው ድርጅት ነው፡፡ ለግል ባለሃብት ተላለፈ ማለት (በተለይ ለውጭ ባለሀብት ከተሰጠ) ይሄንን ገንዘብ ይዞ ወደ ሀገሩ ከመሄድ ባሻገር በእኛ ሀገር ‹ኢንቨስት› የሚያደርግበት ምክንያት የለውም፡፡ የግል ባለሀብቱ ኢትዮጵያዊ ነው ብንልም እንኳ ገቢውን ለልማት ያውለዋል ለማለት ያስቸግራል፣ በዚህም ምክንያት ለልማት ይውል የነበረው ገንዘብ ይቀንሳል፡›› በማለት ያስረዳሉ፡፡\n\nከዚህ ባሻገር እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ያሉ ‹በሰራተኞቻቸው የዓመታት መስዋዕትነት› ለትርፍ የበቁ ተቋማትን ለግል ለማስተላላፍ መሞከር ‹ሀገርን መከፋፈል› ነው ሲሉም ይቆጫሉ፡፡ \n\nየአቶ ክቡር ገናን ስጋት የሚጋሩ ወገኖች ጨምረው ከሚያነሷቸው ስጋቶች አንዱ እነዚህ ድርጅቶች በግል ባለሀብቶች በመያዛቸው ምክንያት የሚሰጧቸው አገልግሎቶች ዋጋ ሊያሻቅብ ይችላል በሚል የሚጠቃለል ነው፡፡\n\nዶ/ር ደምስ ጫንያለው የዋጋ ማሻቀቡ የሚፈጠር ከሆነ ጫናው በሰራተኛው ማህበረሰብ ዘንድ እንዳይበረታ የሚያደርግ መላ ይጠቁማሉ፣ ‹‹በግል ዘርፉ ውስጥ ተሳታፊ ሰራተኞች የሚያገኙት ገቢ የሚመለከት የፖሊሲ ርምጃዎችን መውሰድ ያስልጋል፡፡ ለምሳሌ የዝቅተኛ ደሞዝ ፖሊሲ የለንም፣ እየጮህን ነው ያለነው፡፡ ፍትሃዊ የጉልበት ዋጋ ተመን ከተቀመጠ የዋጋ ጭማሪ አያስፈራንም፣›› በማለት ጭማሪው በግልም ሆነ በመንግስት ሾር ተቀጥሮ ከሚሰራው ሰራተኛ የገቢ ሁኔታ ጋር የተስማማ እንዲሆን መጣር እንዳለበት ይመክራሉ፡፡ \n\nኢትዮ-ቴሌኮምን የመሳሰሉ ተቋማት ከመሰል የጎረቤት ሀገር ድርጅቶች የአገልግሎት ክፍያ ጋር... ", "passage_id": "92ef9f1e76c7f9a1d588cd7916f86b58" }, { "passage": " ዓለማየሁ ገዳ (ዶ/ር) ባለፉት ሦስት መጣጥፋቸው የነጋድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ “መንግሥት እና ሕዝብ አስተዳደር” የተሰኘ መጽሐፍ ላይ ተመሥርተው፣ የገብረሕይወት ምጣኔ ሀብታዊ ኀቲት ግንባር ቀደም መሆኑን እንዲሁም የጀመርናዊው ሔንሪ ቻርለስ ኬሪ ትንታኔ ተፅዕኖ እንዳሳደረባቸው በተጨማሪም ገብረሕይወት ውስጣዊ እና ውጪያዊ የምጣኔ ሀብት ተግዳሮቶች አድርገው ያሰፈሯቸውን አትተዋል። በዚህ ማጠቃለያቸው የገብረሕይወት ትንታኔ ተፅዕኖን በኢትዮጵያን ምሁራን ዘንድ ተመልክተው ጽሑፋቸውን ይቋጫሉ። በመጨረሻም ነጋድራስ ይህንን ውጫዊ የልማት መሰናክል ያልኩትን (የወጪና የገቢ ንግድ አለመመጣጠን) ለማጠቃለል ዓለማቀፍ ገንዘብ ነክ ጉዳዮችን ይዳስሳሉ። በዚህ ትንታኔያቸዉ ካፒታል (ገንዘብ) ከአገር አገር የሚዞረው የተሻለ ትርፍ ፍለጋ መሆኑን በመተንተን በኢኮኖሚክስ ጥናቶች ውስጥ ገንኖ የታወቀውን የፕሮፌሰር መንደልና ፍላሚንግ ሞዴል (ምንም እንኳ የእንገሊዙ ሊቅ ዴቪድ ሪካርዶና ካርል ማርክስ ቀደም ብለው ያሉት ጉዳይ ቢሆንም) ነጋድራስ ቀድመው ጠቁመውታል። እነመንደል ይህንን ሐሳብ አገኙ የተባለው ከ50 ዓመት በኋላ በ1960ዎቹ ነበር። እንደ ገብረሕይወት አተናተን ይህ ዓይነቱ ትርፍ ፈላጊ ካፒታል ተጠናክሮ እንዲመጣ በጊዜው ያለው የሥራ ክፍፍል ደረጃ ዋንኛው ምክንያት ሲሆን፥ ይህ ግን ያገር ውስጥ ኢንደስትሪ እንዳያድግ ዕንቅፋት እደሚፈጥር አትተዋል። ይህ ትንተና ከመሠረተ ልማት ግንባታ ጋር የተቆራኘ መሆኑን የገብረሕይወት ሞዴል ያሳያል። ይህም ለየት ያደርገዋል። በገብረሕይወት አስተሳሰብ ዕወቀት በሌለው ኅብረተሰብ የመሠረት ልማት መስፋፋት ካፒታል ወደ አገሩ ዘልቆ እንዲገባ በማድረግ የአገር ውስጥ ዕደ-ጥበባትን በማኮስስ እና የብድር ጫናን በማጠናከር ያላደገውን አገር በአደገው አገር የመበዝበዝ ሁኔታ ያጠናክራል። ከዚህ ትንትኔ በመነሣት ያገር ውስጥ ምርትን በማጠናከር ራስን በራስ የመቻል ዓላማ ሊኖር እንደሚገባና ይህም የሚከተሉትን የፖሊሲ አቅጣጫዎች በመከተል ሊተገበር እንደሚገባ አስረድትዋል። እነዚህም አንደኛ፣ ተገቢ የሆኑ የቀረጥ ፓሊሲ፦ የአገር ውስጥ የኢንዱስትሪ ምርትን የሚያበረታታና ከወጪ የሚመጠትን ምርቶች የሚገድብ፤ ሁለተኛ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ ማካሔድ፤ እና ሦስተኛ፣ የመዋዕለ ንዋይ ፍሰትን በአግባቡ በመቆጣጠር ማበረታታት ናቸው። የመጨረሻውን ነጥብ ሲያጠናክሩም ገብረሕይወት የሚከተለውን ብለዋል፦ “መቼም የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያስፈልገውን ዕቃ ሁሉ የሚገዛው ከውጭ አገር ሰዎች ነው። ሠራተኞቹ ያሉበት ቦታ ሩቅ ስለሆነ ግን እቃውን አገኛለሁ ሲል ብዙ ትርፍ እና ድካም ይሔድበታል። ጥቅሙን የሚያገኙት ግን ነጋዴዎች ናቸው። ስለዚህ የውጭ አገር ሰዎች ድካማችንን መውሰዳቸው ላይቀር አጠገባችን እየሠሩ ቢወስዱት ይሻላል።” (ገጽ 98) ይህ አተናተንና የፖሊሲ ምክር ለአሁኑ መንግሥታችን ጭምር (ወይ ሐሳቡ ዘመን ተሻጋሪ ሆኖ ወይ እኛ ባለንበት ቆመን) ትምህርት መሆኑን ሳላሠምርበት አላልፍም። ሁለት የዘመኑ ምሁራን ከገብረሕይወት ሼል ጋር ባላቸው ቁርኝነት ሊጠቀሱ የሚገባ ነው። እኚህም ብላታ ደሬሳ አመንቴና አቶ ሚካኤል ተሰማ ናቸው። እኚህ ምሁራን በዘመኑ ዕውቅ በነበረው የ“ብርሃንና ሠላም” ጋዜጣ ላይ ከኢትዮጵያ የዕድገት ችግር ጋር የተያያዙ ብዙ ቁም ነገሮችን ተንትነዋል። ሆኖም እዚህ የጠቃቀስኩት ከገብረሕይወት ጋር የሚያያዘውን ብቻ ነው። ከብላታ ደሬሳ ብንጀምር ከጃፓን ልምድ በመማር በኢትዮጵያ ልማት ለማምጣት ዕውቀት (ትምህርት) ማስፋፋት ቁልፍ እንደሆነ ያብራራሉ። ይህ ግን ዘላቂነት እንዲኖረው ተቋማትና ስርዓት መዘርጋት ወሳኝ እንደሆኑ ተንትነዋል። ለዕውቀት የሠጡት ቦታ በገብረሕይወትም የተተኮረበት ሲሆን ገብረሕይወትም ስርዓት ያላት ትንሽ አገር ስርዓት ከሌለው ትልቅ አገር ሙያ ትሠራለች። ኃይል ስርዓት እንጂ የሠራዊት ብዛት አይደለም ሲሉ ይህንኑ የብላታ ደሬሳ ሐሳብ ተንትነውት ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ሁለቱም ለመሠረተ ልማት መስፋፋት የሰጡት ትኩረት እና በዕቃዎች ዋጋና በገንዘብ አጠቃቀም ላይ ያለው ተፅዕኖ ትንተናቸው ሁለቱም የሚገናኙበት ጉዳይ ነው። ብላታ ሾለ አንፃራዊው የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ጥቅም በተለይም ከአውሮፓው አቻው ጋር ሲታይ የማሽቆልቁሉ አዝማሚያ ላይ ያረጉት አሐዛዊ ትንታኔም በገብረሕይወት ሐሳብና ቀደምት ተመሳሳይ ሼል ላይ ተንተርሰው የሠሩት ይመስላል። ከብላታ ደሬሳ በተጨማሪ የገብረሕይወት ሐሳብ ከሚካኤል ተስማም የ“ብርሃንና ሠላም” ትንተና ጋር ይያያዛል። ሚካኤልና ገ/ሕይወት ለዕወቅት ያላቸው ትኩረትና ስንፍናን በማስወገድ ላይ ያላቸው አመለካከት ተመሳሳይ ነው። በሌሎች አቅጣጫ ግን ሰፋ ያለ ልዩነት አላቸው። ለምሳሌም ሚካኤል ዓለም ዐቀፍ ንግድ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ መሆኑን ሲከራከሩ ገብረሕይወት በታቀራኒው የቆሙ ነበሩ። ገብረሕይወት የገቢ ስርጭት ሁኔታ ሲያሳስባቸው ሚካኤል ግን ይህ ፍታሐዊ የክፍያ ስርዓት ነው ይላሉ። በአጠቃላይ ሲታይ ሚካኤል የኢኮኖሚ ፅንፀ ሐሳቦችን በሕዝቡ ውስጥ በሚገባው ቋንቋ ለማስረፅ ቢጥሩም (ለመጀመሪያ ጊዜ የምጣኔሀብት አስተሳሰቦችን በስዕላዊ ሰንጠረዥ ባማርኛ ጋዜጣ ላይ በመሥራት ጭምር)፣ ከኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር ለማዛመድና ጠለቅ ብለው ለመተንተን እንደ ገብረሕይወት የደከሙ አይመስልም። ይህ ከላይ የጠቀስኩት ገብረሕይወት በዘመኑ ከነበሩ ኢትዮጵያዊ የምጣኔሀብት ተንታኞች ጋር ያለው ቁርኝት መሠረታዊ ገጽታ ሲሆን ጽሑፌን ከማጠቃላሌ በፊት ግን የገብረሕይወት አስተሳሰብ ከጊዜ ሒደት አንፃር ሲታይ ምን መልክ እንደሚይዝ ለመጠቆም እወዳለሁ። እስካሁን ባየነው የገብረሕይወት ሞዴል ገለጻዬ ውስጥ ዛሬ ወይም ዘንድሮ የሆነው ነገር፣ ነገና ተነገ ወዲያ ወይም በሚቀጥለው ዓመት/ጊዜ ሊያመጣ የሚችለውን ተፅዕኖ (ፈረንጆቹ ‹ዳይናሚክስ› የሚሉትን በአማርኛ “ተገሳጋሽነት” ልንለው የምንችለው) ትኩረት አልሰጠሁትም ነበር። እውነታው ግን የገብረሕይወት ሼል የጊዜ ሒደት በልማት ላይ ያለውን ተፅዕኖ (ተገሳጋሽነትን) በአንክሮ ያጤነ ነው። ሙሉዕ በሆነው የገ/ሕይወት ምስለ ኢኮኖሚ የዛሬው ግጭት በሰው ኃይል ሀብት ላይ ያለው አሉታዊ ተፅዕኖ ዛሬ ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን መጪውን ጊዜ/ዓመታት ያካትታል። በተመሳሳይም የዛሬው የንግድ ልውውጥ መዛባት ተፅዕኖ ዛሬ ላይ ብቻ ሳይወሰን ለሚቀጥሉት ዓመታትም የሚዘልቅ ነው። የነዚህ ድምር ውጤት (የኢኮኖሚው ተገሳጋሽነት) የዛሬውን ምርታማነትና ምርት ላይ ተፅዕኖ ማሳደር ብቻ ሳይሆን የመጪው ጊዜ ምርትና ምርታማነትም ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል። ስለሆነም የመፍትሔ ሐሳብ ፍለጋው ዘመን ተሻጋሪ መሆን አለበት ማለት ነው። ይህ አስተሳሰብ ከአንዱ ተማሪዬ (ከአብረሃም አበበ) ጋር በቅርቡ እንዳደረግነው ጠለቅ ባለ የሒሳብ ቀመር ሲሠል የገብረሕይወትን የጠለቀ አስተሳሰብ ጥርት አድርጎ ያሳያል። በተጨማሪም ገብረሕይወት ያነሱትን መሠረታዊ የልማት ችግሮች አጥጋቢ መፍትሔ ለመስጠት መንገዱን ይከፍትልናል። አጥርቶ ማየት ደግሞ የመፍተሔ ፍለጋ ‹ሀሁ› ነው። ለማጠቃለል ያህል፣ በዚህ አጭር ጽሑፌ አንባቢ የነጋድራስ ሼል ምን ያህል ጥልቅና ድንቅ እንደሆነ እንደሚረዳልኝ ተስፋ አደርጋለሁ። በተለይም ደግሞ ‘ልማታዊ የምጣኔሀብት ትንታኔ” በሚባለው የምጣኔሀብት ትምህርት ፈርጅ ድንቅ የተባሉትን ግኝቶች ነጋድራስ ገብረሕይወት ግኝቶቹ ተገኙ ከተባለበት 40 ና 50 ዓመት በፊት እንደጻፏቸው አንባቢው ይገነዘባል። በሁለተኛ ደረጃ የነጋድራስ አስተሳሰቦች ድሮ ተሠርተው ታሪክ ሆነው የሚቀሩ ሰነዶች ብቻ እንዳልሆኑ ለማሳየት ሞክሪያለሁ። ነጋድራስ የዛሬ መቶ ዓመት ገደማ የኢትዮጵያ መሠረታዊ ችግሮች ብለው ምሁራዊ ትንታኔና የፖሊሲ አቅጣጫን ያሳዩባቸው ጉዳዮች በሚያሳዝንና በሚያሳፍር መልኩ ዛሬም ከእኛ ጋር ያሉ፥ ዛሬም ምክራቸውን ያልተጠቀምንበት መሆኑ ነው። እንግዲህ ይሄንንም ሐሳብ በተቻለኝ አቅም ለማሳየት ሞክሬያለሁ። በመጨረሻም የነጋድራስ ሐሳቦች የረቀቁና የመጠቁ ስለሆኑ ለብዙ ምርምሮችና የፖሊስ ሐሳቦች በር ከፋች መሆናቸውን ላሠምርበት እፈልጋለሁ። ተመራማሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች ይህንን አቅጣጫ ቢከተሉና የፖሊሲ አቅጣጫቸውንም በዚህ ተንተርሰው ቢያዩ ዛሬም ፍሬያማ ሼል ሊሠሩበት እነደሚችሉ በማስገነዝብ ጽሑፌን በዚሁ አጠቃልላለሁ።ዓለማየሁ ገዳ (ዶ/ር) በአ.አ.ዩ. የምጣኔ ሀብት ፕሮፌሰር ናቸው። በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ሊገኙ ይችላሉ።ቅጽ 1 ቁጥር 4 ኅዳር 29 ቀን 2011", "passage_id": "9a17bf8b862495f97429a086501e965b" }, { "passage": "“ሕዝቡ ለግድቡ ግንባታ የሚችለውን እያደረገ ቢሆንም ሜቴክ ግን ሕዝቡ በእኛ ላይ ያለውን እምነት አሳጥቶናል”\nኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ያለውን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ በገንዘብ ለመደገፍ በርካታ አማራጮች ተዘርግተዋል፡፡ የቦንድ ሽያጭ እና የ8100 A የአጭር መልዕክት የድጋፍ ማሰባሰቢያ መንገዶችም ከነዚህ አማራጮች መካከል ናቸው፡፡\nየግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ከ2003 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ወርሃ ሰኔ 2012 ዓ/ም ድረስም ከሃገር ውስጥ የቦንድ ሽያጭ እና ከልገሳ ከ12 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ተሰብስቧል እንደ ግንባታው ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት መረጃ፡፡\nከአል ዐይን አማርኛ ጋር ቆይታ ያደረጉት የጽሕፈት ቤቱ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም እንደገለጹት ከዳያስፖራ የቦንድ ሽያጭና ልገሳ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሲገኝ ከልዩ ልዩ ገቢዎች ደግሞ ከ244 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል፡፡\nእስካሁን በነበረው የገቢ አሰባሰብ ሂደት በጥቅሉ 13 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገደማ ገንዘብ እንደተሰበሰበም ነው አቶ ኃይሉ የተናገሩት፡፡\nግንባታውን በዐቅማቸው ለመደገፍ ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ ሁሉ ሲገለገሉበት የነበረው የ8100 A የሞባይል የአጭር መልዕክት ገቢ የማሰባሰቢያ ዘዴ ይህን ገቢ በማሰባሰብ ረገድ የጎላ አስተዋጽኦን አበርክቷል፡፡\nሁሉም የዐቅሙን በቀላሉ እንዲያበረክት በማስቻል ረገድም የማይናቅ ድርሻ ነበረው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያንና የግንባታው ደጋፊዎችም በዚሁ ዘዴ የድጋፍ እጃቸውን ዘርግተዋል፡፡\nበተጀመረበት አመት 80 ሚሊዮን ብር ለማሰባሰብ ያስቻለው አማራጩ በ2008 ዓ.ም ደግሞ 48 ሚሊዮን ብር አስገኝቷል፡፡\n“ሜቴክ ሕዝቡ በእኛ ላይ ያለውን እምነት አሳጥቶናል”አቶ ኃይሉ ሕብረተሰቡ ግንባታውን ለመደገፍ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ የተጀመረው ሾል ከፍተኛ ፈተና ገጥሞት እንደነበር ያነሳሉ፡፡ ይህም የግድቡን የኤሌክትሮ መካኒካልና የሃይድሮ ስቲል ስትራክቸር ሼል ለመስራት ኃላፊነቱን ተረክኖ የነበረው የብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን(ሜቴክ) ኃላፊነቱን በወጉ ካለመወጣቱ እና መስራት የነበረበትን ሾል በወቅቱ በተገቢው መንገድ ባለማጠናቀቁ ነው፡፡ በዚህም ሕብረተሰቡ ከፍተኛ ጥርጣሬ ውስጥ ገብቷል፡፡\n“በተሰራው ስህተት ገንዘባችን ተበላ” የሚል ከፍተኛ ቅሬታ ድጋፍ ሲያደርግ ከነበረው የህብረተሰብ ክፍል ሲቀርብ እንደነበርም ነው ዳይሬክተሩ የገለጹት፡፡\n“በጽ/ቤቱ የምንሰራ ሰዎች ጋር እየደወሉም ጭምር ‘ገንዘባችንን አከሰራችሁት፣ ጠላቶቻችን እናንተ ናችሁ’” የሚሉ ዛቻዎች ይደርሷቸው እንደነበርም ያስቀምጣሉ ምንም እንኳን ጽህፈት ቤቱ የሚሰበሰበውን ገንዘብ በቀጥታ ወደ ፕሮጀክቱ ገቢ የሚደረግ ቢሆንም፡፡\nከሁለት ዓመት በፊት የተደረገው የአመራር ለውጥ ግን በግድቡ ዙሪያ የነበሩ ችግሮችን ለመፍታትና የሕዝብን አመኔታ ለመመለሾ አግዟል እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም መንግስት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን አከናውኗል፡፡ ተደጋግመው የሚሰሙ የ‘ለግድቡ የተዋጣው ገንዘብ ተበልቷል፣ ለታቀደው ነገር አልዋለም’ መሰል አስተያየቶችን ለማስተካከል የሚያስችሉ ተጠያቂነት የማስፈን ስራዎች መጀመራቸውንም የተናገሩት፡፡\nቀደም ሲል በተጠቀሱት ምክንያቶች ተቀዛቅዞ የነበረው የሕዝብ ተሳትፎ አሁን ላይ ተመልሶ እየተነቃቃ መሆኑን ያነሱት አቶ ኃይሉ በተጠናቀቀው ወርሃ ሰኔ 2012 ዓ/ም ብቻ ከ87 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡\n", "passage_id": "74332553e947dbbc3ea7c3b92c76a120" }, { "passage": "የኢኮኖሚ ምሁራን የካፒታል ገበያን አስፈላጊነት ከሀብት ክፍፍልና ከኢኮኖሚ ፋይዳው አንጻር አጉልተው ያነሱታል። በሌላ በኩል፤ ለታዳጊ አገራት አያስፈልግም፤ በገበያው የሚሳተፉት ኩባንያዎች ውስን ስለሚሆኑ ለልማት የሚያመጣውም የረባ ጥቅም የለም ሲሉ የሚሞግቱ ምሁራንም አሉ። የአፍሪካ ንግድ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ክቡር ገና የካፒታል ገበያ ለኢትዮጵያ አያስፈልግም ይላሉ። እንዲህ የሚሉበት ምክንያትም አንደኛ፤ በተለያዩ ምክንያቶች በካፒታል ገበያ (ስቶክ ኤክስቼንጅ ማርኬት) የሚሳተፉ ኩባንያዎች ውስን ይሆናሉ የሚል ስጋት ስላላቸው ነው። በገበያው ላይ ለመሳተፍ ከሚያስፈልጉ መስፈርቶች መካከል ሕጎችና ደንቦች ማክበር፤ ታክስ በአግባቡ መክፈልና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሂሳብ አያያዝ መኖር የሚሉት ይገኛሉ። በኢትዮጵያ እነዚህን መስፈርቶች የሚያሟሉ ኩባንያዎች በጣም ውስን ናቸው። አብዛኛዎቹ ኩባንያዎች ታክስ በመፍራት ብዙ አተረፍን ማለት አይወዱም። በዚህ ምክንያት ብዙ ኩባንያዎች በካፒታል ገበያ ውስጥ ላይሳተፉ ስለሚችሉ የገበያው አስፈላጊነት ብዙም አይደለ ይላሉ። በጥቅሉ የካፒታል ገበያ እንደየአገሩ፤ ጊዜውና አስፈላጊነቱ ሊለያይ ቢችልም፤ በታዳጊ አገራት በገበያው የሚሳተፉ ድርጅቶች ውስን በመሆናቸው ለልማትና ለሀብት ክፍፍል የሚኖረው ሚና አናሳ ነው፤ የሚል መከራከሪያም ክቡር ገና ያነሳሉ። ለምሳሌ፤ የካፒታል ገበያ ያላቸው የአፍሪካ አገራት ለኢኮኖሚው ሊወራለትና ሊጻፍ የሚችል ጥቅም እያገኙ አይደለም። ምክንያቱ ደግሞ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ ኩባንያዎች ያላቸው የፋይናንስ ሥርዓት የተዝረከረከ ነው። 19 የአፍሪካ አገሮች የካፒታል ገበያ አላቸው። በተለይ የደቡብ አፍሪካው ከታዳጊ አገሮች አኳያ ትልቅ ገበያ ቢሆንም፤ በዓለም ካሉት ትላልቅ የካፒታል ገበያዎች ተርታ ግን አይመደብም። በሌሎቹ የአፍሪካ አገራት ያሉት 18 የካፒታል ገበያዎችም በጣም ትንንሽ የሚባሉ ናቸው። ምክንያቱም፤ የሚንቀሳቀሱት የተወሰኑ ድርጅቶችን ይዘው ነው። የገበያ ካፒታላቸውና እንቅስቃሴያቸውም በጣም አነስተኛና ውስን በመሆኑ ኢኮኖሚያዊ ጥቅማቸውም እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። በኢትዮጵያም ገበያው ቢኖር ከዚህ የተለየ ሊሆን አይችልም ብለዋል። ሁለተኛ፤ የካፒታል ገበያ ለውጭ ኩባንያዎች ከተፈቀደ አክሲዮኖችን በመሸጥ የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ ለሌላ ልማት ሊውል ይችላል የሚል መከራከሪያ ነጥብ ቢነሳም ውሃ የሚያነሳ እሳቤ አይደለም፤ ሲሉ ክቡር ገና ይሞግታሉ። ምክንያቱም በካፒታል ገበያው የውጭ ባለሀብቶችን ለመሳብ ትልልቅ ኩባንያዎች ያስፈልጋሉና፤ ‹‹የፌር ፋክስ አፍሪካ ፈንድ›› የተባለ የአሜሪካ ኢንቨስትመንት ዓለም አቀፍ ኩባንያ ሊቀመንበር አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ፤ የካፒታል ገበያ ለኢትዮጵያ አያስፈልግም የሚለውን የክቡር ገናን ሃሳብ ይቃወማሉ። ግልጽ የሆነ የሂሳብ አያያዝና በቂ ድርጅቶች ስለሌሉ የአክሲዮን ገበያ አያስፈልግም የሚለው ሃሳብ ተቀባይነት የለውም።‹‹ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም›› እንደሚባለው ሁሉም ነገሮች አልተሟሉም ብሎ ቁጭ ማለት ተገቢ አይደለም። ምክንያቱም በአሁኑ ጊዜ ያሉት ኢንቨስትመንቶች ከፍተኛ ካፒታል የሚጠይቁ ናቸው። አሁን ባለው ሁኔታ ለምሳሌ፤ በኢትዮጵያ በካፒታል (አክሲዮን) ገበያው ላይ መስፈርቱን አሟልተው የአክሲዮን ድርሻ (ሟር) መሸጥ የሚችሉት ትልልቅ የግል ኩባንያዎችና መንግሥት ወደ ግል የሚያዛውራቸው ድርጅቶችንም ጨምሮ 16ቱ ባንኮችና 16ቱ\nኢንሹራንስ ድርጅቶች ናቸው። ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግባቸውና በብዙ መቶ ሺህ የአክሲዮን ድርሻ የሸጡ ናቸው። የኢትዮጵያ ባንኮች በ25 ዓመታት ጊዜ\nውስጥ አክሲዮን በመሸጥ ማሰባሰብ የቻሉት 30 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። ይህ በጣም ትንሽ ገንዘብ ነው። ከሰሀራ በታች ሦስተኛ ትልቅ ኢኮኖሚ ያላት ኢትዮጵያ ናት። ይህም ሆኖ የኢትዮጵያ ባንኮች አጠቃላይ ካፒታላቸው አንድ ቢሊዮን ዶላር ነው። እናም የተደራጀ የካፒታል ገበያ በሚኖርበት ጊዜ በቀላሉ የአክሲዮንን ድርሻ (ሟር) በመሸጥ ከፍተኛ ካፒታል መሰብሰብ ይችላሉ። እናም በገበያው ላይ የሚሳተፉ ኩባንያዎች ውስን ናቸው ብሎ አያስፈልግም ከማለት፤ በተወሰኑት ድርጅቶች ተጀምሮ ቀስ በቀስ ሌሎች ኩባንያዎች እየተዘጋጁና ጥቅሙን እያዩ ሲሄዱ ወደ ገበያው እየተቀላቀሉና እየበዙ ይሄዳሉ፤ ሲሉ አቶ ዘመዴነህ ይሞግታሉ። ሌላው የክቡር ገና መከራከሪያ ነጥብ ደግሞ በኢትዮጵያ አብዛኛው ሰው የአክሲዮን ድርሻ በእጁ የለም። የካፒታል ገበያ ያስፈልጋል የሚሉትም የአክሲዮን ድርሻ በእጃቸው ያለና የተለየ ደረጃ የተቀመጡ ውስን ግለሰቦች ናቸው። እነዚህ ግለሰቦች በፈለጉ ጊዜ የአክሲዮን ድርሻቸውን ወደ ገንዘብ ሊቀይሩ የሚችሉበት መንገድ ስለሌለ ይህ ይመቻች የሚል ሃሳብ ነው የሚያነሱት። ለዚህ ብቻ የሚውል የካፒታል ገበያ ደግሞ ምንም ጥቅም አይኖረውም። አቶ ዘመዴነህ በተጨማሪ፤ የካፒታል ገበያ አሁን አያስፈልግም የሚለውን የክቡር ገናን ሃሳብ አይቀበሉትም። በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ካፒታል የሚፈልጉ ብዙ የግል ኩባንያዎች አሉ። ለምሳሌ፤ በአሁኑ ጊዜ ሕጋዊና ግልጽ ባልሆነ መንገድ የባንክና የኢንሹራንስ የአክሲዮን ድርሻ በየቀኑ እየተገዛና እየተሸጠ ነው። እናም ሕጋዊና የተደራጀ የካፒታል ገበያ አስፈላጊነት ጥያቄ ውስጥ የሚገባ አይደለም። ሌላው፤ መንግሥት እንደ ኢትዮ ቴሌኮም፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድና ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉ መሰል የመንግሥት ትልልቅ ኩባንያዎች አክሲዮናቸው እንዲሸጥ ወስኗል። ተቋማቱ በአዲስ አበባ የካፒታል ገበያ ላይ ቢሸጡ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የኢትዮ ቴሌኮም የአክሲዮን ባለድርሻ መሆን ይችላሉ። ለዚህ ነው የካፒታል ገበያ የሀብት ክፍፍል ያመጣል የሚባለው። ክቡር ገና የካፒታል ገበያ አያስፈልግም ሲሉ ሌላም ማጠናከሪያ ሃሳብ አላቸው። በአሁኑ ጊዜ የካፒታል ገበያ በኢትዮጵያ የሚፈለገው ኢንቨስትመንት እንዲስብ ነው። ምክንያቱም፤ ኢንቨስተሩ የአክሲዮን ድርሻውን ይሸጣል ወይም ይገዛል። ሆኖም ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንት እያደገ ከሚገኝባቸው የዓለም አገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ ናት። በኢትዮጵያም ብዙ ኩባንያዎች መጥተው ፋብሪካ እየከፈቱ ይገኛሉ። እናም በዚህ ሁኔታ ኢንቨስትመንትን መሳብ ከተቻለ የካፒታል ገበያው መኖር የሚያመጣው ብዙም ለውጥ አይኖርም። አቶ ዘመዴነህ የዓለም አቀፍ ኩባንያዎችን ከመሳብ አኳያ የተለየ አተያይ አላቸው። ብዙ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ኢንቨስት እያደረጉ ነው። ለምሳሌ፤ ዲያጆ ኬንያና ናይጀሪያ ባሉት የንግድ ተቋማቱ የአክሲዮን ድርሻውን በሁለቱ አገር ባለው የአክሲዮን ገበያ ይሸጣል። በዚህም ናይጀሪያውያንም ሆኑ ኬንያውያን የአክሲዮን ድርሻ የመግዛት ዕድል አላቸው። በኢትዮጵያም የካፒታል ገበያ ቢኖር የዓለም አቀፍ ኩባንያዎችን ድርሻ (ሟር) በመግዛት ኩባንያው ከሚያተርፈው ትርፍ ውስጥ የድርሻቸውን ያህል የመጠቀም ዕድል ይኖራቸዋል። ሌላው በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ኩባንያዎች ለመቋቋም፤ ለማደግና በዓለም ገበያ ላይ ተወዳዳሪ ለመሆን ካፒታል ይፈልጋሉ። በሕግ የተቋቋመ፤ ልክ የምርት ገበያ የግብርና ምርቶችን እንደሚያገበያየው ሁሉ ለአክሲዮኖች ድርሻ የሚሸጥበትና የሚገዛበት የተደራጀ ገበያ ቢኖር የሕዝቡን፤ በተለይ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች ተጠቃሚነት ከፍ ያደርጋል። ጊዜንም ይቆጥባል። በአጭር ጊዜ ውስጥም ብዙ ካፒታል ማሰባሰብ ያስችላል፤ ሲሉ አቶ ዘመዴነህ የካፒታል ገበያን ጥቅም ያብራራሉ። የፋይናንስ ባለሙያው አቶ ዛፉ እየሱስ ወርቅ ዛፉ በበኩላቸው፤ የካፒታል ገበያ አስፈላጊነት የሚያከራክር ጉዳይ አይደለም ይላሉ። ምክንያቱም ካፒታል ለማሰባሰብና ትልቅ ኩባንያዎችን ለመፍጠር የካፒታል ገበያ ትልቅ ጥቅም አለው። ለዚህም ነው በአሁኑ ጊዜ መንግሥት የካፒታል ገበያ እንዲፈጠር እየተቀሳቀሰ የሚገኘው ብለዋል። የአቶ ዘመዴነህ ምክረ ሃሳብ የካፒታል ገበያ ከመጀመሩ በፊት የኢንቨስተሩን ጥቅም የሚጠብቅና በየቀኑ የሚደረገውን ግብይት የሚቆጣጠር የመንግሥት ድርጅት ያስፈልጋል። ገበያውን ሥርዓት የሚያሲዙ ሕግና ደንቦች መውጣት አለባቸው። ኩባንያዎች ወደ ካፒታል ገበያ በሚመጡበት ጊዜ ፈቃድና ክህሎቱ ያላቸውና በደንበኛቸው ስም በየቀኑ የአክሲዮን ድርሻ የሚገዙና የሚሸጡ የአክሲዮን ደላሎች ያስፈልጋሉ። ኩባንያዎቹ የአክሲዮን ድርሻ ከመሸጣቸው በፊት ለገበያ ብቁ መሆናቸውን መስፈርት የሚያዘጋጅ የኢንቨስትመንት ባንክ መቋቋም አለበት የሚል ነው። በኢትዮጵያም በ1952 ዓ.ም\nየአክሲዮን ማህበራት የሚተዳደሩበት የንግድ ሕግ ወጥቶ የስኳር ፋብሪካዎች የአክሲዮን ድርሻዎችን በመሸጥ የአክሲዮን ገበያ ቢጀመርም ብዙ ርቀት ሳይጓዝ በደርግ መንግሥት ተቀጭቷል። ኢትዮጵያ ገበያ መር ኢኮኖሚ መከተል ከጀመረች ከ1985 ዓ.ም ወዲህ እስካሁን ድረስ አንድ ሺህ የሚደርሱ የአክሲዮን ማህበራት ቢኖሩም ማህበራቱ የአክሲዮን ድርሻቸውን መሸጥ ቢፈልጉ የሚሸጡበት የካፒታል ገበያ (የስቶክ ኤክስቼንጅ ማርኬት) የለም። በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ እኤአ 2020 ኢትዮጵያ ውስጥ የካፒታል ገበያ እንደሚኖር ይፋ አድርገዋል። ስለዚህ፤ በካፒታል ገበያ ለመሳተፍና የጥቅሙ ተጋሪ ለመሆን የሚፈልጉ ኩባንያዎች ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ አለባቸው። መንግሥትም በእጁ የሚገኙትን ትልልቅ ተቋማት በየደረጃው ወደግል ይዞታ እንደሚያዛውር በያዘው እቅድ መሠረት የካፒታል ገበያ የሚጀመርበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይኖርበታል። ከፍታ ያለው ማንኛውም ህንፃ የአሳንሰር ወይንም ተመሳሳይ አገልግሎት ሊኖረው ይገባል ብለዋል። ነገር ግን እነዚህና መሰል አዋጆች ተግባራዊ ባለመሆናቸው ዜጎች በተለይም አካል ጉዳተኞች በየጊዜው ደህንነታቸው አደጋ ላይ ሲወድቅ ይታያል። የየዕለት እንቅስቃሴዎቹ ሁሉ በዊልቸር እገዛ የሆነው አካል ጉዳተኛ ወጣት አቤኔዘር እዝቅኤል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪ ነው። ወጣቱ እንደገለፀውም፤ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥም ሆነ ከግቢ ውጪ ያለው እንቅስቃሴ በተለይም ለአካል ጉዳተኞች እጅግ ፈታኝ ነው። አጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ ብዙ ችግሮች አሉ። አካል ጉዳተኞች በየትም ቦታ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ለመንቀሳቀስ የሚያስችል ምቹ ሁኔታአዲስ ዘመን መጋቢት18/2011\n\n\n\n\n\nďż˝I`wWFËŠ", "passage_id": "3212e6d0b5755748b70a595f590784a0" }, { "passage": "በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የመንግሥት እና የሕዝብ ንብረት አላግባብ ሲባክን እየተመለከቱ ዝም የሚሉት ሰዎች ቁጥር ጥቂት አይደለም፤ አንዳንዶቹ ሲባክን እያዩ በዝምታ ከመመልከት እና በአሉባልታ ከማንሳት በስተቀር የራስ ንብረት እንደባከነ ቆጥረው ሲጠይቁ እንኳን አይታዩም፡፡የመንግሥት አሠራሮች እንዲስተካከሉም የሚጠይቀው ሰው ከዚህ ግባ የሚባል አይደለም፤ በየቤቱ ጉዳዩን ከመተቸት ባለፈ ለምን ብሎ የሚጠይቅ ያለ አይመስልም፡፡በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ያነጋገርናቸው ግለሰቦች እንዳሉት በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች አካባቢ ያሉ አንዳንድ አሠራሮች የሕዝብን ሀብት ያላግባብ የሚያባክኑ መሆናቸውን እንደታዘቡ ነግረውናል፡፡በክልሉ አንዳንድ የልማት ተቋማት ተሠርተው ለምረቃ በሚበቁበት ወቅት እና የእንግዳ ማስተናገጃ በሚል የሚወጣው የመንግሥት እና ሕዝብ ሀብት  ከተሠራው ሼል  በላይ ሆኖ የሚያዩበት ሁኔታ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡ግለሰቦቹ እንደራሳቸው ንብረት አይተው ለምን ብለው መጠየቅ እንዳልቻሉ እና ይህን ባለማድረጋቸው ተገቢ እንዳልሆነ እንደሚያምኑም ነግረውናል፡፡አስተያየት ሰጭዎቹ አሁን ላይ በመንግሥት በኩል ያለውን ክፍተት አይቶ የተወሰደው ርምጃ ጥሩ ቢሆንም አሁንም በተለያዩ ሁኔታዎች የሚባክነውን ሀብት መቆጣጠር የሕዝብም የመንግሥትም ኃላፊነት ነው ብለዋል፡፡የአማራ ብሔራዊ ሀገር አቀፍ ዜና መንግሥት ምክር ቤት በተሻሻለው የክልሉ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ ሦስት እና 10 ላይ እንደተብራራው የክልሉ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ትብብር ቢሮ ክልሉ የሚያጸድቀውን በጀት ለክልሉ ልማት እንዲውል እና ብክነቱንም ቁጥጥር እንዲያደርግ እና የተለያዩ የአሠራር መመሪያዎችን  እንዲያወጣ ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡", "passage_id": "08db2dce01bd74a16b5ccbb2bfb58309" } ]
768bc1e928c421258b9560d4546e56bc
fbbfabafb2c778d2fbe510b89f50771d
ምክር ቤቱ ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬታማነት የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዳማ፡- በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ውጤታማ እንዲሆን ድጋፍ እንደሚደረግ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ አስታወቁ። በንግድ ስርዓት ማሻሻያ፣ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት አተገባበርና ኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለማድረግ እየተከናወኑ ባሉ ሥራዎች ዙሪያ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የተዘጋጀ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ትላንት በአዳማ ከተማ ተጀምሯል።የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በወቅቱ እንደገለጹት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ውጤታማ እንዲሆን በትብብር መሥራት ይገባል። ምክር ቤቱ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ማፅደቁን የገለጹት አፈ ጉባኤው ለስምምነቱ ውጤታማነት ምክር ቤቱ ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል። በንግድ ዘርፉም ሆነ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ማሻሻያው የታሰበለትን ውጤት እንዲያመጣ ምክር ቤቱ የህግ ማዕቀፎችን ከማሻሻል ጀምሮ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ አመላክተዋል። “በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያስተሳስር መሰረተ ልማት ቁልፍ ሚና አለው” ያሉት አፈ ጉባዔው ከኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ጅቡቲና ሌሎች ሀገራት ጋር እየተከናወነ ያለው የመሰረተ ልማት ትስስር ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቀጣይም ህጎችና አሠራሮችን በመፈተሽ ማሻሻያ የማድረግ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አፈጉባኤው ጠቁመዋል። በሀገሪቱ ለተጀመረው የንግድ ዘርፍ ስር ነቀል ለውጥ ከህግ አውጪው ጀምሮ ሁሉም በቅንጅት መሥራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በመድረኩ የተሳተፉ የምክር ቤቱ አባላት በጉዳዩ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲይዙ በማድረግ በቀጣይ ለሚሠሩ ሥራዎች ውጤታማነት ተገቢው ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ አፈ ጉባኤው አስታውቀዋል። የሀገሪቱን የንግድ ስርዓት ለማዘመን እየተሠራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተወካይ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ናቸው።የውጪ ንግድን ማሳደግ፣ የገበያ መዳረሻዎችን ማስፋት፣ ምርትና ምርታማነትን መጨመር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር ማሳደግና ማስፋፋት ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም አምባሳደር ምስጋኑ ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እንዲሳካ፣ ከመጪው ጥር ወር ጀምሮ ተግባራዊ ከሚሆነው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ተጠቃሚ እንድትሆንና የዓለም የንግድ ድርጅት አባል የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አመልክተዋል። “ውህደቱ በሚፈጥረው ምቹ ሁኔታ ሀገሪቱ የተሻለ አገልግሎት እንድታገኝና ተወዳዳሪ እንድትሆን ጭምር እየሠሩ መሆናቸውንም አምባሳደር ምስጋኑ ተናግረዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37635
[ { "passage": "\nኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም በአፍሪካ በማረጋገጥ አህጉር~አቀፍ ኢኮኖሚያዊ ትስስር እንዲፈጠር ጥረቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን አስታውቀዋል።\nበሶስተኛ ቀን ቆይታ በስዊዘርላንድ ዳቮስ \"የአፍሪካ ሰላም ግንባታ\" በሚል ርዕስ የአፍሪካ መሪዎችን በአንድ መድረክ ያሰባሰበ የገፅ ለገፅ ውይይት ተካሂዷል።\nበዚህ ውይይት ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ፤ ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም በአፍሪካ በማረጋገጥ ጠንካራ አህጉር~አቀፍ ኢኮኖሚያዊ ትስስር እንዲፈጠር እየሰራች ያለውን ስራ ና ጥረት አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል።\nበምስራቅ አፍሪካ ሃገራት መካከል ሰላማዊ ድባብ እንዲሰፍን እና የተረጋጋ የኢኮኖሚ መስተጋብር እንዲፈጠር በኢትዮጵያ ያልተቋረጠ ጥረት ተስፋ ሰጪ ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል።\nኢትዮጵያ የጀመረችውን የለውጥ ጉዞ የሚገዳደሩ ፈተናዎችን በአስተውሎት ለመሻገር እና አስተማማኝ ሰላም ለመገንባት ፅኑ አቋም እንዳላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።\nበመድረኩ የታደሙት የተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት መሪዎች በሰጡት አስተያየት፤ የአህጉሪቱን ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር የማጥበቅ አጀንዳ ወቅታዊ ምላሽ የሚሻ መሆኑን አስምረውበታል።\nአፍሪካ ከሌሎች ክፍለ~አህጉራት ጋር ሊኖራት የሚገባውን ኢኮኖሚያዊ ትብብር በሚጠበቀው ከፍታ አለመጠናከሩ ከፊትለፊት ብዙ ስራ እንደሚጠይቅ በችግሩ ውስብስብነት ዙሪያ መሪዎቹ ተግባብተዋል።\nከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ተፈጥሮ የነበረው ችግር በዘላቂነት ለመፍታት እና በቀጠናው የተረጋጋ ሰላም ለመገንባት የተደረሰበትን ውጤት በመልካም ተሞክሮነት ቀርቧል።\nበተመሳሳይ ሌሎች የአፍሪካ ሃገራት የኢትዮጵያን ውጤታማ ተሞክሮ ከነባራዊ ሁኔታዎች ጋር መቃኘት እንደሚገባ በመጠቆም ትርጉም ያለው አህጉር ዓቀፍ ኢኮኖሚያዊ ትስስር በጋራ ለመፍጠር እንደሚተጉ መሪዎቹ መግባባት ላይ ደርሰዋል።\n\nበሌላ በኩል ጠንካራ ዓለማቀፋዊ የኢኮኖሚ ትስስር ለመፍጠር ኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ እና ትራንስፖርት አገልግሎት ስርዓትን የማዘመን ስራ እያከናወነች መሆኑንም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን አስታውቀዋል።\nበስዊዘርላንድ ዳቮስ በተ.አ.ኤ አዘጋጅነት የሎጅስቲክስ እና ትራንስፖርት አገልግሎት ስርዓት ዙሪያ ዓለምአቀፍ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።\nበመድረኩ ላይ የታደሙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ፤ ኢትዮጵያ ዓለማቀፋዊ የኢኮኖሚ ትስስር ለመፍጠር የሎጅስቲክስ እና ትራንስፖርት አገልግሎት ስርዓትን ለማዘመን በትኩረት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።\nመንግሥት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማጠናከር በርካታ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑምን በዝርዝር አንስተዋል።\nኢኮኖሚያዊ የማሻሻያ ስራዎች መካከል የሎጅስቲክስ እና ትራንስፖርት አገልግሎት ስርዓትን ለማዘመን በመንግስት የተወሰዱት እርምጃዎች የግሉን ዘርፍ የሚያተጋና የሚያነቃቃ መሆኑን ጠቁመዋል።\nከተለያዩ ክፍለ አህጉራት ጋር ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለመፍጠር ደረጀቸውን የጠበቁ መሰረተ ልማት እና አገልግሎቶች በሂደት እንደሚመቻችም ነው የገለጹት።\nበመድረኩ የተሳተፉ የተለያዩ ሃገሮች የፖለቲካ እና የቢዝነስ መሪዎች፤ ኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ እና የትራንስፖርት ዘርፍ ለማዘመን የሄደችበት ርቀትን አድንቀዋል። በቀጣይ ኢትዮጵያ በሎጅስቲክስ እና በትራንስፖርት ዘርፍ በሚፈጠር ጠንካራ ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ትስስር በቅርበት እንደሚሰሩ ፍላጎታቸውን ገልፀዋል።\nበተያያዘ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የኤሚሬቶች ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሼክ አህመድ ቢን ሰኢድ አል ማክቲም ጋር በሎጂስቲክስ እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።\n", "passage_id": "089b4e80d47a1bc2d12fc6c364270b17" }, { "passage": "•የልማት አጋሮችና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አካላት ለማሻሻያው ተግባራዊነት ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋልአዲስ አበባ፡- ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃግብሩ ምቹ የቢዝነስ ሁኔታን በመፍጠርና የተዛባውን ማክሮ ኢኮኖሚ በማስተካከል ኢትዮጵያ በ2030 የአፍሪካ ብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን እንደሚያስችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለፁ፡፡ ማሻሻው ለኢትዮጵያ እድገት ወሳኝ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ድጋፍ እንደሚያደርጉም የልማት አጋሮችና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ አባላት አረጋግጠዋል፡፡ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ\nማሻሻያ መርሃግብሩን በተመለከተ\nትናንት በተባበሩት መንግስታት\nየአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን\nየስብሰባ አዳራሽ ለልማት\nአጋሮች እና ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ትውውቅ በተደረገበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እንደገለፁት፣ መንግስት ተዳክሞ የነበረውን ኢኮኖሚ እንዲያንሰራራ ለማድረግ በርካታ ስራዎች መስራቱን ጠቁመዋል፡፡ ይህ ማሻሻያ ለኢትዮጵያ ብልፅግና ጉዞ እንደ ድልድይ የሚያገለግል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ለተግባራዊነቱም የልማት አጋሮች የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ‹‹መርሃግብሩ ምቹ\nየቢዝነስ ሁኔታን በመፍጠርና\nየተዛባውን ማክሮ ኢኮኖሚ\nበማስተካከል ኢትዮጵያ በ2030\nየአፍሪካ ብልፅግና ተምሳሌት\nእንድትሆን ያስችላል፡፡›› ያሉት\nጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የኢኮኖሚእድገቱ ሁሉንም ተጠቃሚ እንዲያደርግ መንግስት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሀፊ ዶክተር ቬራ ሶንግዊ፣ መንግስት ማሻሻያውን ተግባራዊ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀው፤ ከመንግስት ጎን በመቆም አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ሳቢ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዳሏት የተናገሩት ዋና ፀሀፊዋ፣ ይህንን እድል ተጠቅሞ በርካታ የስራ እድሎችን በመፍጠር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለመደገፍ የልማት አጋሮች የራሳቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ተናግረዋል። በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣\nየሱዳንና ደቡብ ሱዳን\nዳይሬክተር ወይዘሮ ካሮሊን\nቱርክ በበኩላቸው፤ መሰል\nየመልማት እቅዶች ከራሱ\nከመንግስት መምጣቱን አድንቀው፤\nኢትዮጵያን ወደቀጣዩ ምእራፍ ለማሸጋገር የውጭ ምንዛሬ አቅምን ማሳደግ፣ የወጪና ገቢ ንግድን ማመጣጠን፣ የኢንቨስትመንት ማሻሻያዎችን መተግበር፣ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግና ሌሎችም ስራዎች እንደሚያስፈልጉ ጠቁመዋል። የዓለም ባንክ ለዚህ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል። ‹‹መርሃግብሩ በደንብ የተጠና እና ወደ እድገት ሊያሸጋግር የሚችል ሲሆን፤ ወደተግባር ለመቀየር የፋይናንስ፣ የአደረጃጀትና አቅም ግንባታ ስራዎች ያስፈልጋሉ።›› ያሉት በኢትዮጵያ የስዊድን ኤምባሲ የሁለትዮሽ እድገት ትብብር ክፍል ሀላፊ ወይዘሮ አኒካ ኖርዲን፣ መንግስት የኃይል አቅርቦትና ኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂን ማስፋፋት ላይ በትኩረት እንዲሰራ ጠይቀዋል። በርካታ የስራ እድሎችን\nመፍጠር ተገቢ መሆኑን\nያነሱት ወይዘሮ አኒካ፣\nየልማት አጋሮች ለዚህ\nማሻሻያ ተግባራዊነትና ለኢትዮጵያ\nኢኮኖሚ ማደግ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። ለቀጣዮቹ አስር ዓመታት ተግባራዊ የሚደረገው ይህ ማሻሻያ፣ በወጣቶች ስራ እድል ፈጠራ፣ በማክሮ ኢኮኖሚ፣ በውጭ ምንዛሬ ክምችት፣ በሃይል አቅርቦትና ሎሎችም በርካታ ዘርፎች ለውጥ ለማምጣት ታቅዶ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት፣ በልማት ባንክ፣ በብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን እና በገንዘብ ሚኒስቴር ቅንጅት የተዘጋጀ ነው። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃግብር በዋናነት ማክሮ ኢኮኖሚያዊ፣ መዋቅራዊና እና ዘርፉን የተመለከቱ ማሻሻያዎች አቅፎ እንዲይዝ ተደርጎ የተዋቀረ ሲሆን፣ ከሳምንት በፊት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከተውጣጡ ተወካዮች፣ ምሁራንና ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር በሸራተን ሆቴል ውይይት ተደርጎበት ግብአት እንደተሰበሰበ የሚታወስ ነው።አዲስ ዘመን ጳጉሜ 5/2011 ድልነሳ ምንውየለት ", "passage_id": "7d9ddd20e2c0ccd5874e564ae39408a8" }, { "passage": "የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጠና ሰኔ 30 ቀን 2011 ዓ.ም በኒጀር ዋና ከተማ ኒያሚ በተካሄደው የኅብረቱ የመሪዎች መደበኛ ጉባዔ መጽደቁ ይታወሳል፡፡ ነጻ የንግድ ቀጣናውን ለመመሥረት የተደረሰውን ስምምነት ኢትዮጵያን ጨምሮ 28 የአፍሪካ አገሮች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው ስምምነቱ አጽድቀዋል። የአፍሪካ አህጉር ነጻ የንግድ ቀጣናን በመጪው ሐምሌ 2012 ዓ.ም በይፋ ሥራ ለማስጀመር 54 የአፍሪካ ኅብረት አባል አገሮች ስምምነቱን መፈረማቸውን የኀብረቱ ኮሚሽን የንግድና ኢንዱስትሪ ኮሚሽነር አምባሳደር ሙቻንጋ አልበርት አስታውቀዋል።", "passage_id": "c89ddcc6826b32e6a340a9213d531f82" }, { "passage": "ራስወርቅ ሙሉጌታአዲስ አበባ፦ በአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ መመስረት የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግና ግሽበትን ለመቀነስ ብሎም የእውቀት ሽግግር እንዲስፋፋ ለማድረግ እንደሚረዳ ተገለፀ። የአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ ትስስር በጥንቃቄ ከተመራ እያንዳንዱን የአፍሪካ ሀገር ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተጠቆመ። በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ዶክተር ደመላሽ ሀብቴ በጋራ የነፃ ገበያ ዙሪያ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በአፍሪካ አገራት መካከል የተቀናጀ የኢኮኖሚ ግንኙነት ባለመኖሩ አህጉሪቱ ከሰማንያ በመቶ በላይ የንግድ እንቅስቃሴዎች እያደረገች ያለችው ከአውሮፓ፣አሜሪካና እስያ አገራት ላይ ጥገኛ በመሆን ነው። በዚህም የተነሳ አህጉሪቱ ደካማ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ፣ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት የሚከሰትባትና ዝቅተኛ የእውቀት ሽግግር የሚስተዋልባት ሆና ቆይታለች። ከዚህ ቀደምም የአፍሪካ አገራት እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ትስስር ለማሳደግ የተሠሩ ጅምሮች ቢኖሩም ውጤታማ ባለመሆናቸው እስከ አሁን እርስ በእርስ ያላቸው ግንኙነት ከሃያ በመቶ የዘለለ አልነበረም ያሉት ዶክተር ደመላሽ፤ በተመሳሳይ ደረጃ የሚገኙ የኢንዱስትሪ ግብአቶችንም ሆነ እንደ ነዳጅ ያሉ ያለቀላቸውን ምርቶች አፍሪካ አገራት ውስጥ በስፋት እየተመረቱ ቢሆንም ሌሎች ተጠቃሚ ጎረቤት አገራት የሚያስገቡት ካደጉት አገራት ነው ብለዋል። በአህጉሪቱ የተጠናከረ የንግድ ልውውጡና የዳበረ የነፃ ገበያ ተፈጥሮ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው የተቀላጠፈ እንዲሆንና በሚጠበቀው ደረጃ እንዲያድግ የአፍሪካ አገራት የንግድ ልውውጥ በጋራ ነፃ ገበያ ሊጠናከርና ሊስፋፋ ይገባዋል ብለዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ መመስረትና ወደተግባር መግባት አፍሪካ እንደ አህጉር ከሌላው ዓለም ጋር ለሚኖራት የንግድና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶች በር የሚከፍት እንደሚሆንም አመልክተዋል። ነፃ ገበያው በአሁኑ ወቅት በስፋት የሚታየውን ወደመካከለኛው ምሥራቅና ሌሎች አገራት የሚደረገውን የሰው ኃይል ፍልሰት ወደአፍሪካ እንዲሆን ያግዛል ያሉት ዶክተር ደመላሽ፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የእውቀት ሽግግሩም በየደረጃው የተቀላጠፈ እንዲሆን ይረዳል፤ በአገራት መካከል የሚኖረውም የዲፕሎማሲ ግንኙነት የተጠናከረ እንዲሆን ያግዛል ብለዋል። የአፍሪካ አገራት የጋራ የነፃ ገበያ ከመሰረቱ ከፈለጉ በዶላር ወይንም በራሳቸው በሀገራቱ የመገበያያ ገንዘብ እንዲሁም እቃ በእቃ የመገበያየት ዕድሉ ስለሚኖራቸው የውጭ ምንዛሬ እጥረትን እንደሚቀንስ ጠቁመው፤ ይህም ሆኖ የመንግሥት ታክስ ሊቀንስ ይችላል እንዲሁም በአገራቱ መካከል የተመጣጠነ ዕድገት ባለመኖሩ የሚፈጠር ጫና ሊኖር እንደሚችል አመልክተዋል።የአፍሪካ የጋራ የነፃ\nገበያ ትስስር በጥንቃቄ\nእየተቆጣጠሩ መሥራት፣ ትልልቅ\nተቋማትን መገንባትና ጥራት\nያላቸውን ምርቶች በማምረት\nለጠንካራ ውድድር መዘጋጀት\nከተቻለ እያንዳንዱ የአፍሪካ\nአገር ተጠቃሚ ይሆናል\nሲሉም ዶክተር ደመላሽ\nተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2013 ", "passage_id": "28261b71f98d88d96d6d45cfc834543c" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 4/2005 (ዋኢማ) – አሜሪካ ከሰሃራ በታች ለሚገኙ የአፍሪካ አገራት የሰጠችውን ነፃ የቀረጥና ኮታ የንግድ ዕድል እንድታራዝምና አህጉሪቱን ተጠቃሚ እንድታደርግ ተጠቀየች። አሜሪካ ከሰሃራ በታች ለሚገኙ የአፍሪካ አገራት የሰጠችው የቀረጥና ኮታ ነጻ የንግድ እድል /የአጎዋ/ 12ኛው ጉባኤ በአዲስ አበባ ተጀምሯል። በጉባኤው ላይ የተገኙት የንግድ ሚኒስትር ድኤታ አቶ ያዕብ ያላ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት አሜሪካ ላለፉት 13 ዓመታት ለአፍሪካ የሰጠችውን ነጻ የንግድ ዕድል ለሚቀጥሉት ዓመታት በማራዘም የአህጉሪቱን የዕድገት ጉዞ ማስቀጠል ይገባታል።አሜሪካ የአህጉሪቱን ምርቶች ያለምንም ቀረጥና ኮታ ወደ አገሯ እንዲገቡ በመፈቀድ ለአፍሪካ ዕድገት ላደረገችው ከፍተኛ ድጋፍና እገዛ ሚኒስትሩ አመስግነዋል። ያም ሆኖ ሚኒስትር ድኤታው እንዳሉት አሜሪካ የሰጠቸውን ዕድል የሚያበቃበትን ጊዜ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር እስከ 2020 ድረስ በማራዘም የአህጉሪቱን ተጠቃሚነት እንድታሳድግ ጠይቀዋል። ጊዜውን በማራዘም ረገድ በአሜሪካ መንግሥት የተለያዩ አካላት መካከል ያለው አመለካከትና አቋም ወጥ ሊሆን እንደሚገባም ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል።የተሰጠውን የንግድ ዕድል በብቃት ለመጠቀም ከሰሃራ በታች የሚገኝ እያንዳንዱ አገር ስትራቴጂ በመቅረጽ ሥራ ላይ የሚውልበትን ሁኔታ መፍጠር እንዳለበትም አሳስበዋል። በአፍሪካ ኀብረት ኮሚሽን የንግድና ኢንዱስትሪ ኮሚሽነር ፋቲማ ሐራም በበኩላቸው አጎዋ በአፍሪካና በአሜሪካ መካከል ያለውን የንግድ ግንኙነት በማሻሻል ረገድ ትልቅ ድርሻ ማበርከቱን አብራርተዋል። ክፍለ አህጉራዊ የንግድ ግንኙነቱ በሴቶችና በወጣቶች ተሳትፎ ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ የመጣ በመሆኑ የንግድ ግንኙነቱ ውጤታማና ስኬታማ እንደሆነም ገልጸዋል። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ2001 ጀምሮ የአጎዋ ፎረም በየዓመቱ በአሜሪካና የአጎአ ተጠቃሚ በሆኑ የአፍሪካ አገራተ ሲካሄድ ቆይቷል። የአጎኣ ጉባኤ ከዚህ በፊት በሞሪሺዬስ፣ በሴኔጋል፣ በጋና፣ በኬንያና በታንዛኒያ መካሄዱ ይታወሳል። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር 2012 ከሰሀራ በታች ያሉ የአፍሪካ አገሮች በጠቅላላው 48 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ምርት ወደ አሜሪካ ቢልኩም ከ2011 ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 35 በመቶ እንዲሁም በ2013 ደግሞ በ23 በመቶ ዝቅ ብሏል። አሜሪካ እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር 2012 ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገሮች 22 ነጥብ 6 ቢሊዮን የሚያወጣ ምርት ልካለች። እንደ ኢዜአ ዘገባ ከ2000 ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ400 በመቶ ዕድገት አለው። ወደ አገሮቹ በብዛት ከላኩት ምርቶች ውስጥ መሳሪያዎች፣ ተሽከርካሪዎች፣ አውሮፕላን፣ ዘይትና ጥራጥሬ ሲሆኑ አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ገበያ ከምታካሂድባቸው አገሮች ውስጥ ደቡብ አፍሪካ፣ ናይጄሪያ፣ አንጎላ፣ ጋናና ኢትዮጵያ ናቸው።", "passage_id": "299b75ea5fa3b0abdd04015accbd2c93" } ]
426f5fe44d52ba8f01e816efa2859f49
864df38eb4c878d290b2b0631b20e1cb
ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2013 ሰላማዊ የመማር ማስተማር እንዲኖር እየሠሩ መሆኑን ገለጹ
 • የኮቪድ-19 መከላከልን ታሳቢ አድርገው ተመራቂ ተማሪዎችን መቀበላቸውንም ጠቁመዋል ፋንታነሽ ክንዴ አዲስ አበባ፡- ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በተደጋጋሚ የሚከሰትን የፀጥታ ችግር ከግንዛቤ በማስገባት በ2013 የትምህርት ዘመን ሰላማዊ የመማር ማስተማር እንዲኖር የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሠሩ መሆኑን የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና ወልዲያ ዩኒቨርሲቲዎች ገለጹ። ዩኒቨርሲቲዎቹ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ኮቪድ 19ን ለመከላከል የተቀመጡ ቅድመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ተመራቂ ተማሪዎችን መቀበላቸውንም አስታውቀዋል።የየዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በዩኒቨርሲቲዎች የሚስተዋል የፀጥታ ችግር በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ እክል ሲፈጥር ቆይቷል። በዚህ ዓመት ግን ያን ዓይነት ችግር እንዳያጋጥምና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲፈጠር እየሠሩ ይገኛል። የወቅቱ ስጋት የሆነው የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ለመከላከልም እየሠሩ ሲሆን፤ ተመራቂ ተማሪዎችን የተቀበሉትም በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተቀመጠውን መስፈርት በማሟላት ነው።የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ካሣዬ ጉተማ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል በተማሪዎች ምክንያት በዩኒቨርሲቲው የሚታዩ የፀጥታ ችግሮች የነበሩ ቢሆንም፤ በ2013 ዓ.ም ያን ዓይነት የፀጥታ ችግር እንዳያጋጥም እና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲፈጠር ለማድረግ ሥራዎችን ሲሠሩ ቆይተዋል። በዩኒቨርሲቲው ከሚሠሩ ሥራዎች በተጓዳኝም በግቢው ውስጥ የፌዴራል ፖሊስ ጥበቃ እያደረገ ይገኛል።እንደ ዶክተር ካሣዬ ገለጻ፤ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የፀጥታ ችግር እንዳያጋጥም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመሆን የዩኒቨርሲቲውን ጥበቃ እና የፌዴራል ፖሊስን በማቀናጀት ለተማሪዎች የግንዛቤ መፍጠር ሥራ ተሠርቷል። ተማሪዎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች የሚገጥማቸው ትንኮሳ ካለ ለሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ሪፖርት ማድረግ እንዳለባቸው ተነግሯቸዋል። ቀጣይ ሌሎች ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው በሚመጡበት ወቅትም በየባቻቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ይሠራል።ከፀጥታ ሥራው ባሻገር የኮቪድ-19 ወረርሺኝን መከላከል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ካሣዬ፤ በዚህም በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሟሉ የተቀመጡ መመዘኛዎችን በማሟላትና ይሄንኑ በማስገምገም ተመራቂ ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር እንደሚችሉ ማረጋገጫ ከተሰጣቸው በኋላ ተማሪዎችን መቀበላቸውን ተናግረዋል። እንደ ዶክተር ካሣዬ ማብራሪያ፤ ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲገቡ የኮቪድ 19 ምር አድርገው እንዲገቡ፤ ኮቪድን ለመከላከል የሚያግዝ ሳኒታይዘር በዩኒቨርሲቲው ተመርቶ ለተማሪዎች እንዲቀርብ ተደርጓል። ከዚህም ባለፈ በኮቪድ ፕሮቶኮል መሰረት በዩኒቨርሲቲው ያሉ የተማሪዎች ማደሪያ፣ መታጠቢያና የመመገቢያ ቦታዎች ተጎብኝተው ብቁ መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን፤ በተለይ ከተማሪዎች ማደሪያ ጋር በተያያዘ በአንድ ዶርም ውስጥ አንድ አንድ ተማሪ ብቻ እንዲመደብ ተደርጓል። በመማሪያ ክፍሎችም ከ20 ያልበለጡ ተማሪዎችንመራ ብቻ በመመደብ የተመራቂ ተማሪዎች የመማር ማስተማር ሥራውን ሲያከናውን የቆየና ተማሪዎቹም እንደሚመረቁ የጠቆሙት ዶክተር ካሳዬ፤ ቀሪ ተማሪዎችን ታህሳስ 15 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚቀበሉ አስታውቀዋል።የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ተፈራ አስናቀ በበኩላቸው፤ በዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሥራው በፀጥታ ችግር እንዳይስተጓጎል በማሰብ በርካታ ሥራዎች ተሠርተዋል። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርም ይሄን ታሳቢ ያደረገ የትምህርትና ስልጠና አማካሪ ምክር ቤት ማቋቋሚያ መመሪያ የላከ ሲሆን፤ ይህን ተከትሎ 30 አባላት ያሉት አማካሪ ምክር ቤት ተቋቁሟል። አማካሪ ምክር ቤቱ የዞኑ አስተዳዳሪ የሚመሩትና የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፀሐፊ የሆኑበት ሲሆን፤ ከከተማው የአገር ሽማግዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ወጣቶች የተካተቱበት ነው።እንደ አቶ ተፈራ ገለጻ፤ አማካሪ ምክር ቤቱ በየጊዜው እየተገናኘ በግቢው ውስጥ ለግጭት ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች መኖራቸውን እየገመገመ የመማር ማስተማር ሥራው በትክክል እንዲቀጥል የሚያደርግ ነው። ምክር ቤቱ በዩኒቨርሲቲው በመገኘት ዝግጅቱ ምን ይመስላል የሚለውን የገመገመ ሲሆን፤ ዩኒቨርሲቲውን ከሚጠብቁ ፌዴራል ፖሊሶችና የግቢው ጥበቃዎች ጋር በመሆን የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በምግብ አቅርቦት፣ በቤተመጽሐፍ በተለይም ደግሞ ከመብራትና ውሃ አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮች ሲኖሩ ያንን መነሻ አድርገው ለግጭትና ለሁከት የሚዳርግ ነገር ሲፈጠር እንደነበር ያስታወሱት አቶ ተፈራ፤ ይህንን ለመፍታት ዩኒቨርሲቲው የራሱ የሆነ የውሃ መስመር እንዲኖረው መደረጉን እና የመብራት መቆራረጥ በሚኖርበት ጊዜም ጀነሬተር ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። ከዚህ ባሻገር በዩኒቨርሲተው ዙሪያ የንግድ ቤቶች መኖራቸውንና በእነዚህ ቤቶች ደግሞ መጠጥ እና ሌሎች አደንዛዥ እጾች ሽያጭ እየተበራከተ እንደመሆኑ፤ እንዲህ ዓይነት ግጭቶች እንዲባባሱ በማድረግ በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ችግር ለማስወገድም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።በጸጥታ ሥራው በተጓዳኝ የኮቪድ 19 መከላከል ሥራ ላይ ትኩረት አድርገው እየሠሩ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተፈራ፤ የመማር ማስተማር ሥራው ኮቪድ 19ኝን በመከላከል እንዲቀጥል በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ተመራቂ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ መሆኑን ተናግረዋል። ኮቪድን ለመከላከል በተዘጋጀው ፕሮቶኮል መሰረት የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን የገለጹት አቶ ተፈራ፤ ሳኒታይዘር በግቢው ውስጥ በማምረት ለተማሪዎችና ለዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብ እንዲቀርብ ተደርጓል። በዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች የተዘጋጀ ማስክም ተሰራጭቷል። ከእጅ ንክኪ ነፃ የሆነ የእጅ መታጠቢያ በየቦታው መቀመጡንም ተናግረዋል። እንደ አቶ ተፈራ ገለጻ፤ ከዚህ በፊት በአንድ ዶርም ውስጥ ስድስት ተማሪዎች ይመደቡ ነበር። በአሁኑ ወቅት ግን ሁለት ተማሪዎች ብቻ እንዲመደቡ ተደርጓል። በመማሪያ ክፍሎችም ሃያ አምስት እስከ ሠላሳ ተማሪዎች ብቻ እንዲማሩ በዩኒቨርሲቲው ሰኔት ተወስኗል። በቤተ መጽሐፍት እና በመመገቢያ አዳራሾችም አስፈላጊውን እርቀት ጠብቀው እንዲስተናገዱ ለማድረግ እየተሠራ ነው። ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ የኮቪድ 19 ምርመራ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር ጠቅሰው፤ በሂደት ችግር ቢፈጠር እንኳን በግቢው ውስጥ ምርመራ እንደሚካሄድ ገልጸዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግም የለይቶ ማቆያ ቦታዎች ተዘጋጅተዋል። በኮቪድ መከላከል ፕሮቶኮል ዙሪያ ከተማሪዎች ጋር ውይይት መደረጉን እና ከተማሪዎች ጋር ቅርብ ግንኙነት ላላቸው ሠራተኞች የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ መሠራቱንም አስረድተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37627
[ { "passage": "አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪ መርሐ ግብር ተማሪዎች ቅበላን እየቀነሰ፣ የሁለተኛና የሦስተኛ ዲግሪዎችን ወደ ማስተማርና ወደ ምርምር እንደሚሸጋገር የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አድማሱ ፀጋዬ ገለጹ፡፡የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ይህን ያስታወቁት ዩኒቨርሲቲው ለመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሚመራበትን ስትራቴጂካዊ ዕቅድ አተገባበርን አስመልክቶ፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. በእሸቱ ጮሌ አዳራሽ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ወቅት ነው፡፡ዩኒቨርሲቲው ወደፊት የምርምር ማዕከል እንዲሆን ከፍተኛ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ፣ ዕውቀት በማመንጨት ችግር ፈቺ የሆኑ የምርምር ሥራዎችን በማከናወን ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች በስትራቴጂካዊ ዕቅዱ መካተታቸውን ዶ/ር አድማሱ አመልክተዋል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘም ከዚህ ቀደም ሲል ያለውድድር የሚመደበው የምርምር ገንዘብ፣ ከአሁን በኋላ ውድድርን መሠረት ባደረገ መንገድ እንደሚመደብ ተገልጿል፡፡ለዚህም ይረዳ ዘንድ ዩኒቨርሲቲው የሴኔት ሕጉን እንዳሻሻለ ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡ ‹‹የሴኔት ሕጉን ማሻሻል ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያት የምርምር ዩኒቨርሲቲ መሆን ካለብን፣ እያንዳንዱ መምህር ምርምር መሥራት አለበት፡፡ የምርምር ውጤቱን በታወቁ ጆርናሎች ማሳተም አለበት፡፡ ከዚህ አንፃር በድሮ የሴኔት ሕጉ ላይ ይህንን የሚያስገድድ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ይህንን አስገዳጅ የሚያደርግ ነገር እናካትታለን፤›› በማለት የሴኔት ሕጉን ለማሻሻል መነሻ ስለሆነው ጉዳይ አስገንዝበዋል፡፡‹‹ሁሉም የዩኒቨርሲቲው መምህራን የኮንትራት ሠራተኞች ናቸው፡፡ ኮንትራታቸው ደግሞ የሚታደሰው በየሁለት ዓመቱ ነው፡፡ ስለዚህ መምህራን ኮንትራታቸው እንዲታደስ የግድ ምርምር ሠርተው ማሳተም አለባቸው፤›› ሲሉም በአዲሱ የሴኔት ሕግ ስለተካተተው አስገዳጅ መሥፈርት ገልጸዋል፡፡ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀው ሁለተኛው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ መጀመሪያ ዩኒቨርሲቲው ከተገበረው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ደካማና ጠንካራ ጎኖችን የገመገመ ከመሆኑም በላይ፣  ከሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜስን ዕቅድ ጋር የተያያዘ እንዲሆን ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑ በወቅቱ ተገልጿል፡፡ሁለተኛው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ሲታቀድ ከመጀመሪያው ዕቅድ የተገኙ ድክመቶችንና ስኬቶችን ከማካተት አንፃር የተሠራ ሥራ ስለመኖሩ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹ትልቁ ችግራችን ከመሠረተ ልማት ጋር የተያያዘ ነው፤›› በማለት እነዚህንም በሁለተኛው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ለመቅረፍ እንደሚሠሩ ገልጸዋል፡፡‹‹የማስተማሪያ መሣሪያዎችና የምርምር ኬሚካሎች፣ የመምህራን ተነሳሽነት እንዲሁም የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን በሥራ ላይ ከማቆየት ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለይተን፣ እነሱን እንዴት አድርገን ነው በሚቀጥለው ስትራቴጂካዊ ዕቅዳችን ላይ ማሳካት የምንችለው የሚለውን ተወያይተናል፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡የምርምር ዩኒቨርሲቲ ለመሆን እንደሚጥር የገለጸው ዩኒቨርሲቲው፣ እ.ኤ.አ. በ2025 ከአፍሪካ ምርጥ አሥር ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ ለመሆን እየሠራ እንደሆነም በወቅቱ ተገልጿል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘም በቅርቡ የዓለም ባንክ ለአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የልህቀት ማዕከላትን ለማቋቋም ባዘጋጀው ውድድር፣ በምሥራቅና በደቡብ አፍሪካ ካሉ አገሮች ጋር ተወዳድሮ ዩኒቨርሲቲው በአራት የትምህርትና የምርምር መስኮች የልህቀት ማዕከል እንዲያቋቁም ገንዘብ ማግኘቱንም ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ1942 ዓ.ም. 33 ተማሪዎችን በመቀበል ሥራ የጀመረ ሲሆን፣ በአሁን ወቅት ከ52 ሺሕ በላይ ተማሪዎችን ያስተምራል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በአጠቃላይ ከስምንት ሺሕ በላይ ሠራተኞች አሉት፡፡ ", "passage_id": "987ab5e2e3acc94731575179f01dbe93" }, { "passage": "የአምቦ፣ ወለጋና ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲዎች በ2013 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅት አድርገናል ብለዋል።የዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚዳንቶች ዩኒቨርሲቲዎቻቸው የኮቪድ-19 ወረርሽኝን አስቀድሞ እየተከላከሉና የተማሪዎችን ደኅንነት እያስጠበቁ ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል ቁመና ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።ባለፈው ዓመት በኮቪድ-19 ምክንያት ትምህርታቸውን አጠናቀው ያልተመረቁ ተማሪዎችን ተቀብሎ አስተምሮ በሁለት ወራት ውስጥ ለማስመረቅም የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔ እየጠበቁ መሆናቸውን ገልፀዋል።\n", "passage_id": "1d937695c6ed10f88d3c8435754446dc" }, { "passage": "በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲጎለብት ተማሪዎች ቅድሚያ ለሰላም ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ገለጹ፡፡ለዋልታ አስተያየታቸውን የሠጡት የዩኒቨርስቲው የሰላም ፎረም አባል ተማሪዎች በሀገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን በሁሉም ሰው ልብና አዕምሮ ላይ መሰራት እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡ተማሪዎቹ  የማህበራዊ ሚዲያ በመከታተል ጊዜን ከማባከን ይልቅ ለመጡበት ዓላማ በመቆም ለሚያስተምራቸው  ቤተሰብና አገር በማሰብ ትምህርት ላይ ትኩረት ሰጥተው ሰላም እንዲሰፍን የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል፡፡በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተማሪዎቹ አክለው ገልጸዋል፡፡በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር መሐመድ አወል የተለያዩ አሉታዊ አጀንዳዎች ያላቸው አካላት ተማሪዎችን የተልዕኮ ማስፈጸሚያና መሸጋገሪያ ድልድይ በማድረግ ሰላም  በማሳጣት ፣ በመንግስት ላይ ጫና ለመፍጠር እንደሚፈልጉ በመግለጽ ተማሪዎችን  ለመጠቀም የሚፈልጉት አካላት ከድርጊታቸውን  እንዲቆጠቡ  ለማድረግ የድርሻቸውን  እንዲወጡ ጥሪ አቅበዋል ፡፡ተማሪዎቹ ዛሬ ካሉበት ደረጃ ተሻግረው ነገ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታ የሚቀመጡ በመሆናቸው በዩኒቨርስቲ ያለውን ህብረ ብሔራዊነት በመጠቀም እርስ በርስ በመተዋወቅ፣ በመተባበርና በመረዳዳት ሊማሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ", "passage_id": "263e3d311dd9c5b301cea09890fe911c" }, { "passage": "በዩኒቨርሲቲዎች አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍንና የተረጋጋ የመማርና መሰተማር እንዲኖር ማስቻሉን ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ዛሬ ከዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት ፤መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ካወጀበት ጊዜ በኋላ በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት በመስፈኑ የመጀመሪያውን የትምህርት አጋማሽ በመልካም የመማር ማስተማር መንፈስ ማጠናቀቅ ተችሏል፡፡ይህም ቀደም ሲል ባንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች ተከስቶ በነበረው አለመረጋጋት በመማር ማስተማሩ ላይ እንቅፋት ይሆናል የሚል ስጋት እንዲወገድ ማድረጉን ነው ያስረዱት፡፡የከፍተኛ ትምህርት ማሕበረሰቡ ሰላማቸው የተናጋባቸው የዓለም ክፍሎችን ተጨባጭ ሁኔታዎች  በማስገንዘብ የሰላምን ዋጋ ይበልጥ ማስገንዘብ  እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡እንደ ዶክተር ሳሙኤል ገለፃ የትምክህት፣ የጠባብነትና የኃይማኖት አክራሪነትን ኋላቀር አስተሳሰቦች በመታገል የከፍተኛ ትምህርቱ ማህበረሰብ እንዲጠየፋቸው በመስራት የሰላምን ዘላቂ ዋስትና ማረጋገጥ እንደሚገባም አስገንዝበዋል ፡፡የከፍተኛ ትምህርት ማሕበረሰብ ሰላምን የሚያውኩ ኃይሎችን በመለየት፣ የችግሮቹን ምክንያትና ውጤቱ ሐሳብን በማፍለቅ በጠረጴዛ ዙሪያ በውይይት መፍታት የሚቻልባቸውን ልምዶች ምሁራዊ ትንታኔ መስጠት ይጠበቅበታልም ነው ያሉት ፡፡ይህን ተግባር አጠናክሮ በመቀጠል የትምህርቱን ማህበረሰብ ለሰላም ዘብ እንዲቆም  ማስቻል እንደሚገባ ሚኒስትር ዴኢታው አመልክተዋል ፡፡", "passage_id": "4a0d721f72b5f5d1354f29ef31a5fc62" }, { "passage": "የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጠናከር ለማስቻል የድርሻቸውን እንደሚወጡ በዩኒቨርሲቲው ዙሪያ ያሉ ነዋሪዎች አረጋገጡ።ነዋሪዎቹ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በተማሪዎች መካከል ግጭት እንዲፈጠርና ወደ ማህበረሰቡ እንዲዛመት የሚፈልጉ ሠራተኞቹን እንዲፈትሽም አሳስበዋል፡፡በዩኒቨርሲቲው ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ ”መንስዔው ለጊዜው እየተጣራ ነው” በተባለው ሁከት የመማር ማስተማሩ ሂደት መስተጓጎሉን ታውቋል።ዩኒቨርሲቲው ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሥራውን ለመጀመር በዙሪያው ከሚገኙ ነዋሪዎች ጋር ተወያይቷል ፡፡የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ያሬድ ማሞ በነዋሪዎቹ የተነሱ ሃሳቦች ለዩኒቨርሲቲው ቀጣይ ሥራ ጠቃሚ በመሆናቸው ራሱን ለመፈተሸ እንደሚጠቀምባቸው ገልጸዋል፡፡”በመረጃና ማስረጃ ላይ የተመሰረተ ሥራ እየተሰራ ይገኛል፤ የሚደበቅና የሚድበሰበስ አንዳችም ነገር የለም” ብለዋል ፕሬዚዳንቱ፡፡", "passage_id": "fcb00faf53a70594fc249ba20e59646d" } ]
c776db9ef0f7066ece305a5805e313ea
c16d7c0fc24e820e65b83e26cdb260b0
ከሀገራዊ የልማት እቅዱ ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር እውነተኛ ዕድገት ማምጣት እንደሚቻል ተጠቆመ
ፍሬህይወት አወቀ አዲስ አበባ፡- ከ10 ዓመቱ ሀገራዊ የልማት እቅድ ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ እውነተኛ ዕድገት ማምጣት እንደሚቻል ተጠቆመ።በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር ዶክተር ሞላ ዓለማየሁ ለአዲስ ዘመን እንደተናገሩት፤ የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር በአስር ዓመቱ አገራዊ ልማት እውነተኛ ዕድገት ማምጣት የሚቻል ሲሆን፤ የሀገሪቱን የ10 ዓመት የልማት እቅድ ማሳካት የሚቻለውም እቅዱን ለማሳካት ከሚሠሩ ሠራዎች ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበቱን መቆጣጠር ከተቻለ ብቻ መሆኑን አመልክተዋል። እንደ ዶክትር ሞላ ገለጻ፤ የ10 ዓመት የልማት እቅዱ ታሳቢ ካደረጋቸው ጉዳዮች አንዱ የሀገሪቱን ዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ ከፍ ማድረግ ላይ ነው። ነገር ግን ከነፍስ ወከፍ ገቢ ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበቱን መቆጣጠር ካልተቻለና ግሽበቱ ከፍ ካለ የህብረተሰቡ የኑሮ ደረጃ እያሽቆለቆለ ይሄዳል እንጂ የታሰበው ዕድገት አይመጣም። ስለዚህ ከ10 ዓመት የልማት እቅዱ ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር ተገቢ ነው። በዚህ ረገድ የ10 ዓመት መሪ እቅድ የሀገሪቱን አጠቃላይ የዕድገት አቅጣጫ የሚጠቁም በመሆኑ፤ ግሽበቱን መቆጣጠር ከተቻለ እውነተኛ የሆነ የሀገር ዕድገትን ማምጣት ይቻላል። ይህ ሲሆን ደግሞ አብዛኛውን የማህበረሰብ ክፍል ተደራሽ ማድረግ የሚችል በመሆኑ ፍትሐዊ የሆነ የሀብት ክፍፍል እንደሚኖርም ነው የገለጹት። ይህ የሀገሪቱን አጠቃላይ የዕድገት አቅጣጫ የሚጠቁም የ10 ዓመት ኢኮኖሚያዊ እቅድ የኦፕሬሽን ዕቅድ አለመሆኑን የጠቆሙት ዶክትር ሞላ እቅዱ ግን ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እጅጉን ጠቃሚ መሆኑንም አስረድተዋል። ከዚህ በፊት የነበረውን ሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መጠናቀቁን ተከትሎ ያንን ማስቀጠል የሚችል የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ መዘጋጀቱም ተገቢነት ያለው ከመሆኑም በላይ ዕቅዱ ጠቋሚ ዕቅድ እንደመሆኑ የሀገሪቱን አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ያሳያልም ብለዋል።ዕቅድ ሲታቀድ ያለፈውን መነሻ በማድረግ እንደሆነ የጠቆሙት ዶክትር ሞላ፤ ይህም ባለፈው ጊዜ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን መለየት የሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል። በመሆኑም መንግሥት ካለፈው ስህተቱ በመማር በሀገሪቱ የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ ላይ ባለሙያዎችን ተሳታፊ ማድረጉ የሚበረታታና መለመድ ያለበት ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል።በሀገሪቱ አጠቃላይ ዕቅድ ላይ ቢቻል ማህበረሰቡን ማሳተፍ ተገቢ መሆኑን ያነሱት ዶክተር ሞላ፤ ከዚህ በፊት በነበረው አሠራር በጉዳዩ ላይ የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሳይሆኑ የመንግሥት ፍላጎት ብቻ እጅግ በተጋነነ ሁኔታ ይስተናገድ እንደነበር አስታውሰዋል። በመሆኑም ይህ የመንግሥትን ፍላጎት ብቻ መሰረት ያደረገ እቅድ ህብረተሰቡን ያላማከለ በመሆኑ ክንውኑ ዜሮ እንደሚሆን ተናግረዋል። በዚህኛው እቅድ ላይም ከባለሙያዎች ባለፈ፣ ምቹ ሁኔታ ካለ በሀገሪቱ ዕቅድ ላይ ህብረተሰቡን ተሳታፊ በማድረግ የእኔ ብሎ እንዲረዳውና የበኩሉን እንዲወጣ ማስቻል፤ ህብረተሰቡን አሳታፊ በሚያደርግ መልኩ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37642
[ { "passage": "የሀገሪቱ ያለመረጋጋት ሁኔታ በቀጣይ አምስት ዓመታት በእያንዳንዱ ግለሰብ የምግብ ፍላጎት ላይ ተጽኖ ሊፈጥር እንደሚችል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እየገለጸ ነው፡፡ባለሁለት “ዲጂት” የምጣኔ ሀብት ዕድገቱም አሁን ላይ እንቅፋት ገጥሞታል፡፡ ይህ ደግሞ በሀገሪቱ ያለውን ከ11 ሚሊዮን በላይ ሥራ ፈላጊ ወጣት ወደ 30 ሚሊዮን እንዳያሳድገው ሥጋት ፈጥሯል፡፡የዓለም ገንዘብ ተቋም በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የኢትዮጵያ የምጣኔ ሀብት ዕድገት ከዘጠኝ በመቶ በታች እንደሚሆን አሉኝ ያላቸውን መረጃዎች አጣቅሶ ተንብያውን አስቀምጧል፡፡ ከአስርት ዓመታት በላይ ከ10 እስከ 12 በመቶ ዕድገት በማስመዝገብ መቀጠሉን ሲነገርለት የነበረው ምጣኔ ሀብት በዚህ ዓመት ግን አሽቆልቁሎ 6 ነጥብ 2 በመቶ እንደሚሆን ነው ድርጅቱ የተነበየው፡፡በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በምጣኔ ሀብት ትምህርት መስክ ረዳት ፕሮፌሰር አንዱዓለም ጎሹ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መረጃን መሠረት አድርገው እንደተናገሩት ለምጣኔ ሀብት ዕድገቱ መውረድ በሀገር ውስጥ ያለው አለመረጋጋት እና በዜጎች መካከል ያለው የሀብት አለመመጣጠን እየሰፋ መሄዱ የራሱ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳረፈ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የብር የመግዛት አቅም እንዲዳከም እርምጃዎች መወሰዳቸውን የጠቀሱት ረዳት ፕሮፌሰር አንዱዓለም ርምጃውም በራሱ አሉታዊ ጫና እንደሚያሳርፍ ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይም ወደ ውጭ ሀገራት ከሚላኩት ምርቶች ይልቅ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡት ብልጫ እንዳላቸው አንስተዋል፡፡‹‹የምጣኔ ሀብት ዕድገቱ ከዋጋ ግሽበት ጋር የተያያዘ አንድምታ አለው፡፡ የዋጋ ግሽበት አንዱ የሚከሰትበት ምክንያት ሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሰው የገንዘብ መጠን (ብር) መጨመር ነው›› ብለዋል፡፡ በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ገንዘብ ሲገታ የኢንቨስትመንት ሥራዎች እንደሚቀንሱና ይህም የምጣኔ ሀብት ዕድገቱ ወደኋላ እንደሚጎትተው አስረድተዋል፡፡በግብርና እና በኢንዱስትሪው ላይ የሚፈሰው መዋለ ንዋይ የምጣኔ ሀብት ዕድገቱን እንደሚወስነው ምሁሩ አስገንዝበዋል፡፡ በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ያለውን የዋጋ ግሽበት ችግር ለመቆጣጠር ባንኮች ለኅብረተሰቡ የሚያበድሩትን የገንዘብ መጠን መቀነስ አንዱ መንገድ እንደሆነም አስገንዝበዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት መንግሥት ባንኮች የሚያበድሩትን የገንዘብ መጠን በመቀነስ ወይም የማበደር አቅማቸውን ለማውረድ ሲሠራ እንደነበርና ይህም ደግሞ ምጣኔ ሀብቱ በፍጥነት እንዳያድግ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ትልልቅ የሀገር ፕሮጀክቶች በገንዘብ እጥረት መጎዳታቸውንም ዶክተር አንዱዓለም ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ልማት ባንክ ያሉት ደግሞ የተበላሸ ብድር (ነን ፐርፎርሚንግ ሎን) አለባቸው፡፡ የፍትሐዊነት ችግርም እንደሚነሳባቸው ምሁሩ ይገልጻሉ፡፡የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ተመራጩ መፍትሔ ምርታማነትን ማሳደግ መሆኑን የገለጹት ረዳት ፕሮፌሰር አንዱዓለም ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ምርት ማሟላት ሥር ነቀል ለውጥ እንደሚያመጣ ነግረውናል፡፡ ሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሰውን ገንዘብ መቀነስ የአጭር ጊዜ ውሳኔ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡ የግል ተቋማትን በሚገባ በማበረታታት ወደ ምርት እንዲገቡ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም መክረዋል፡፡የምጣኔ ሀብት ዕድገቱ በማሽቆልቆል ጉዞው የሚገፋበት ከሆነ የዋጋ ግሽበት ጋር በተገናኘ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች የበለጠ ተጎጂ ይሆናሉ፤ ይህም ድህነት እንዲንሰራፋ ያደርጋል፡፡የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ወደ ግሉ ዘርፍ ማዞር ውጤታማ እንደሚያደርግ ረዳት ፕሮፊሰሩ አንስተዋል፡፡ የመንግሥት ቁጥጥር ተተግብሮ ድርጅቶቹን ለባለሀብቶች በመስጠት ወደ ግሉ ዘርፍ ማዞር ውድድርን በመጨመር አዎንታዊ ተፅዕኖ እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በፊት መንግሥት የውጭ ምንዛሬ ላይ ቁጥጥር ያደርግ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ በገበያ እንዲተመን ታስቧል፡፡ ይህም የብርን የመግዛት አቅም የበለጠ እያዳከመ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ዋጋ ያሻቅባል፡፡ ይህ በኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ላይ ጫና ማሳረፉ የማይቀር ይሆናል፤ የኢንዱስትሪውን ዘርፍም ያቀጭጫል፡፡በራስ አቅም ማምረት እንዲቻል በትምህርቱ ዘርፍ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ መዋለ ንዋይ በማፍሰስ በራስ ምርት የራስን ፍላጎት ማሟላት እንደሚቻልም አስረድተዋል፡፡ፖለቲካዊ መረጋጋት በማምጣት፣ ሠላምን ሙሉ በሙሉ በማረጋገጥና በማስቀጠል በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶችን ወደ ኢንዱስትሪው ዘርፍ መሳብ እንደሚቻልም አስገንዝበዋል፡፡ የምጣኔ ሀብት ዕድገት ጥቅል የሀገር ውስጥ ምርት ታይቶ ብቻ ሳይሆን የዜጎች ኑሮ ሲሻሻል በመሆኑ የሕዝቡ የምግብ ፍላጎት መሟላት፣ ጤና፣ ትምህርትና ሌሎች አገልግሎቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሠራም አሳስበዋል፡፡ መሠረተ ልማት የማስፋፋት ሥራው ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡የግብርናውን ምርት፣ ለኢንዱስትሪ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች፣ ምቹ የሥራ ሁኔታ እና አምራች ኢንዱስትሪው ከመንግሥት የሚፈልጉትን እንደ ኃይል አቅርቦትና መሠል ጉዳዮች ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የምጣኔ ሀብት ትንበያውን እንደሚያወጣ የተናገሩት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ታደለ ፈረደ ናቸው፡፡ ተባባሪ ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያ በንግድ ሥራ ምቹነት ከ190 ሀገራት በ159 ደረጃ ላይ መስፈሯንም ተናግረዋል፡፡የዋጋ ንረቱ ደግሞ ምጣኔ ሀብቱን ሊያዳክም እንደሚችል አመላክተዋል፡፡ የማምረቻ ጥሬ ዕቃዎች እንዲወደዱ በማድረግ የወጋ ጭማሪ እንዲከሰት እንደሚያደርግ ነው ያመላከቱት፡፡ ወጪን በመጨመር መሸጥ የማይቻልበት ደረጃ ላይ እንደሚያደርስ ተባባሪ ፕሮፌሰር ታደለ አስገንዝበዋል፡፡ለዋጋ ንረቱ ዋናው መንስኤ የአቅርቦት ችግር መሆኑን ያነሱት ተባባሪ ፕሮፌሰር  ታደለ በሀገር ውስጥ ምርት ራስን ለመቻል ብዙ ርቀት መጓዝ እንደሚጠበቅ አሳስበዋል፡፡ የገንዘብ መመሪያ (ፖሊሲ) ቁጥጥር ሥርዓቱ የዋጋ ንረቱን ችግር ይፈታል የሚል አመኔታ እንደሌላቸውም ገልጸውዋል፡፡ እንዲያውም ‹‹ፍላጎትን ይገታል››ብለዋል፡፡ ግብርናው እንዲሻሻልም ሆነ እንዲዘምን እየተሠራ አለመሆኑ ችግሩን እንደሚያገዝፈውም ገልጸውልናል፡፡ በመስኖ የሚመረተው ሰብል ከዚህ ግባ የማይባል መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችም በውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ችግር እንደተጋረጠባቸው ጠቅሰዋል፡፡", "passage_id": "4a9a5300319bd7673647b46c8c3e6ad3" }, { "passage": " የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጣጠር በአቅርቦት ላይ አጽንኦት ሰጥቶ እንደሚሰራ መንግሥት አስታውቋል፡፡ በአቅርቦት ላይ ለመስራት የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ለማግኘትም የግሉን ዘርፍ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይጠቁማሉ፡፡የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ዶክተር ቆስጠንጢኖስ በርሄ አቅርቦቱ ላይ ለመነጋገር የመንግሥት እቅድ በዝርዝር መውጣት እንደሚኖርበት ጠቅሰው ‹‹ስንዴ፣ ስኳር ፣ዘይት እና በሀገር ውስጥ ሊመረቱ የሚችሉትን ሁሉ ማምረት አለብን፡፡››ይላሉ፡፡እንደ ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ገለጻ፤ በአቅርቦቱ ላይ ለመስራት የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት አለማግኘት ትልቁ ተግዳሮት ሊሆን ይችላል፡፡ለእነዚህ የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ሀገሪቱ አሁን ከወጪ ንግድ፣ከእርዳታ ፣ከብድር እና ዜጎች ለቤተሰብ ከሚልኩት በሚገኝ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት ማሳካት እንደሚያዳግት ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ይገልጻሉ፡፡እነ ኬንያ ያላቸው የመሬትና የውሃ መጠን በጣም ትንሽ መሆኑን፣ኤክስፖርታቸው ግን በጣም ከፍተኛ መሆኑን ያመለክታሉ፡፡ አብዛኛው ኤክስፖርታቸው ከአግሮ ኢንዱስትሪ ጋር የተያያዘ መሆኑን በማመልከትም ሀገራችን እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ የማትችልበት ሁኔታ እንደማይኖር ይጠቁማሉ፡፡የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ክቡር ገና ግሽበቱን ከፍ አድርገውታል ከሚባሉት አንዱ የመኖሪያ ቤት የኪራይ ዋጋ እየጨመረ መምጣት መሆኑን በአብነት ጠቅሰው፣ ‹‹ይሄ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚቃለል አይደለም፤ የእህል ዋጋው ሊረጋጋ የሚችለው ገና ተመርቶ እንደመሆኑ አሁን ላለው ችግር መፍትሄ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም›› ይላሉ፡፡ለአቅርቦቱ መጨመር ግብአቶች፣ መሳሪ ያዎች፣ የውጭ ባለሙያ፣ ቁሳቁስ ፣ወዘተ ሊያስ ፈልጉ እንደሚችሉ ጠቅሰው፣ ለእዚህ ግዥ የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት የወጪ ንግዱ የወደቀበትን ምክንያት በቅድሚያ ማጥናት እና መፍትሄ ማስቀመጥ እንደሚገባ ይገልጻሉ፡፡ ለወጪ ንግዱ መቀዛቀዝ አንዱ ምክንያት የዓለም ገበያ ዋጋ መውደቅ ሊሆን እንደሚችል ጠቅሰው፣ የምርጥ ጥራት ችግር፣የሀገሮች እና ኩባንያዎች የተሻለ ምርት ይዞ መቅረብ፣ባለፉት ዓመታት የተከሰተው አለመረጋጋት ይህን ተከትሎ በኩባንያዎች ላይ የደረሰው ጉዳትም ምክንያት ሊሆኑ እንደሚችሉ በመጥቀስ እነዚህን ማስተካከል እንደሚገባ ያስገነዝባሉ፡፡ ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ከሀገር ውስጥ ባለሀብቶች አብዛኛዎቹ በንግድና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ መሆናቸውን ጠቅሰው፣በእርሻ እና በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩት የውጭ ባለሀብቶች እንደሆኑ ይናገራሉ፡፡ አቶ ክቡር የዶክተር ቆስጠንጢኖስን ሀሳብ በማጠናከር የሀገሪቱ የግሉ ዘርፍ የተጎዳ መሆኑን ይጠቅሳሉ፡፡የግል ዘርፉ ከፍተኛ እድሳት እንደሚያስፈልገው፤የንግድ ምክር ቤቱም አቅም ማማከር የሚችል መሆን እንዳለበት ያስገነዝባሉ፡ ፡በዚህ ውስጥ የመንግሥት ሚና ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ከፍተኛ እንደሆነም ነው የሚናገሩት፡፡ እንደ አቶ ክቡር ገለጻ፤ያለመንግሥት ንቁ ተሳትፎ ይህን ኢኮኖሚ ማንቀሳቀስ አይቻልም፡ ፡ በኢኮኖሚ ከፍተኛ ደረጃ የደረሱ አገሮች አሁን ሀገሪቱ ያጋጠማትን አይነት ችግር ሲገጥማቸው መንግሥታቱ ኢኮኖሚውን ማንሳት ባለባቸው ሁኔታ ላይ በትኩረት ይሰራሉ፡፡ የመንግሥት ፕሮጀክቶች ሲጀመሩ የግሉም ዘርፍ እንደገና መንቀሳቀስ እንደሚጀምር አቶ ክቡር ተናግረው፣በዚህም ኢኮኖሚው ነፍስ እንዲዘራ ማድረግ እንደሚቻል ይጠቁማሉ፡፡ ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ሀገሪቱ አስፈላጊዎቹ የውጭ ባለሀብቶች እንደሌሏት፣ የመጡትም ጥለው የሚወጡባት መሆኗን ጠቅሰው፣ መንግሥት የውጭ ባለሀብቶች ምንም ሳይሰሩ የሚወጡበትን ሁኔታ በአስቸኳይ ማስተካከል እንደሚኖርበት ያስገነዝባሉ፤‹‹ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን ሽግግር እስከምንፈጽም ድረስ እነዚህ ካፒታል ይዘው የሚመጡ ባለሀብቶች ያስፈልጉናል›› ይላሉ፡፡ ሀገሪቱ የቅባት እህሎች ወደ ውጭ እየላከች የምግብ ዘይት ከውጭ ለማስመጣት ከ450 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማውጣት እንደሌለባት የሚናገሩት ዶክተር ቆስጠንጢኖስ፣ካፒታሊስቶችን በማምጣት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከማሟላት ባሻገር ለውጭ ገበያ ማቅረብ እንደሚኖርባትም ያመለክታሉ፡፡ ዶክተር ቆስጠንጢኖስ እንደሚሉት፤ይህችን ሀገር ሊያሳድጉ የሚችሉ ኢንቨስተሮች መምጣት የሚችሉት በሀገሪቱ ሌላው ዓለም የደረሰበት የፋይናንስ ስርዓት ሲኖር ብቻ ነው፡፡የፋይናንስ ስርዓቱን ማሻሻል ከተቻለ የውጭ ባንኮች ካፒታል ይዘው የሚመጡበት ሁኔታ ይፈጠራል፤በዚህም የግሉን ዘርፍ ማሳደግ እንዲሁም ኢንዱስትሪዎች በከፍተኛ ሁኔታ እንዲሰሩ ምቹ ሁ ኔታ መፍጠር ይቻላል፡፡ ‹‹ኢንቨስተሮች በኪሳቸው ዶላር ጠቅጥቀው አይመጡም፡፡ሊያበድራቸው የሚችል ባንክ እያሰቡ ነው የሚመጡት፡፡››ሲሉ ገልጸው፣ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ካደረጉት አብዛኛዎቹ የቱርክ፣ ቻይናና ህንድ ባለሀብቶች ከልማት ባንክ ለመበደር የመጡ መሆናቸውን ይገልጻሉ ፡፡ አቶ ክቡር ባለሀብቶችን በመሳብ ሂደት ‹‹ምን አይነት የውጭ ኩባንያ ነው እንዲገባ የሚፈለገው የሚለው መጀመሪያ መታየት አለበት›› ይላሉ፡ ፡ የዶክተር ቆስጠንጢኖስን ሀሳብ በማጠናከርም የውጭ ባለሀብቶች ከሀገር ውስጥ ባንኮች መበደር እንደሌለባቸው ይናገራሉ፡፡‹‹የውጭ ባለሀብት ካፒታል ይዞ መምጣት ይኖርበታል፣በስንት መከራ የተጠራቀመውን የውጭ ምንዛሪ መሻማት የለበትም፤ አሁን የተያዘው ግን መሻማት ነው፡፡ ››ሲሉ ይገልጻሉ፡፡ ዶክተር ቆስጠንጢኖስ እርሻ በትንሽ ነገር እንደሚበላሽ ጠቅሰው፣በዚህ ዘርፍ ላይ ይበልጥ መስራት የሚቻለው በተለይ የሰፋፊ እርሻ ሥራ ልምድ ካላቸው ሀገሮች ባለሀብቶችን በማምጣት መሆኑን ይጠቁማሉ፡፡ በእነዚህ ባለሀብቶች ወጣቶችን ማሰራት እንደሚቻልም ይገልጻሉ፡፡ አቶ ክቡር ሀሳብ በማጠናከር እርሻ ለኢንቨስትመንት በጣም አስቸጋሪ ዘርፍ መሆኑን በመጥቀስ የዶክተር ቆስጠንጢኖስን ያጠናክራሉ፡፡ የግሉ ዘርፍ ሊሰማራበት የማይገባ ዘርፍ በማለትም ከዶክተር ቆስጠንጢኖስ የተለየ ሀሳብ ይሰነዝራሉ፡፡ የግል ባለሀብቱ በራሱ ገንዘብ እርሻ ውስጥ መግባት እንደማይፈልግም ይገልጻሉ፡፡ የእርሻ ኢንቨስትመንት ቢሰጥ የሚሻለው በአካባቢው ለሚኖረው ህብረተሰብ መሆን እንዳለበት አቶ ክቡር ይጠቁማሉ፡፡አርሶ አደሩ ለዘመናት ያካበተው የግብርና እውቀት እንዳለው በመጥቀስ የዶክተር ቆስጠንጢኖስን ሀሳብ ያጠናክራሉ፡፡ የአርሶ አደሩንና የህብረት ሥራ ማህበሩን አቅም በስልጠናና በመሳሰሉት ድጋፎች በማጠናከር በግብርና ኢንቨስትመንቱ እንዲሰማሩ ማድረጉ የተሻለ እንደሚሆን ይጠቁማሉ፡፡ ‹‹በሀገሪቱ አሁን ብዙ ነገሮች እየተቀየሩ ናቸው፡፡›› የሚሉት ዶክተር ቆስጠንጢኖስ፣ የልማት ባንክ አስተዳደር እንደገና በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራ ፣የብድሩ ሁኔታም እየተስተካከለ ነው››ሲሉ ጠቅሰው፣ሀገሪቱ ኢንቨስትመንትና ንግድን በቀላሉ ከመጀመር አንጻር ያለችበትን ዝቅተኛ ደረጃ ለመለወጥ መንግሥት እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም መልካም ተግባር ብለውታል፡፡ ዶክተር ቆስጠንጢኖስ እንደሚሉት፤ባለሀብቶች ማስተዳደር ላይ በስፋት መስራት ያስፈልጋል፤የውጭዎቹንም ሆነ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን ብቃት ባላቸው ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያውያን ከሌሉም የውጭ ሀገር ዜጎች መጥተው እንዲያስተዳድሯቸው ማድረግ ይገባል፡፡ ባለሀብቶቹ ተመልሰው የሚሄዱበት ምክንያት ምንድን ነው፡፡መጀመሪያ ማነው ያመጣቸው?ሲመጡ ምን አይነት ምዘና እና ድጋፍ ያደርግላቸዋል? የሚሉት ጥያቄዎችም መመለስ እንደሚኖርባቸው ይጠቁማሉ፡፡ከመሰረተ ልማት ጀምሮ እስከ ጸጥታ ማስከበር ድረስ ያለው ችግርም መታየት እንዳለበት ይጠቁማሉ፡፡ የፋይናንስ ሥርዓቱ ይሻሻል ሲባል ልቅ ይሁን ማለት እንዳልሆነም ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ጠቅሰው፣ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ የሚያስችሉ ብቃት ያላቸው ትላልቅ ሬጉሌቲንግ ኤጀንሲዎች ሊኖሩ እንደሚገባም ያመለክታሉ፡፡‹‹ሬጉላቶሪ ኤጀንሲ ማለት ማስቆም አይደለም፤ህጉን ተከትለው መሄዳቸውን መከታተል ነው፤ህጉን ከመጣሳቸው በፊት መምከር ነው›› ሲሉም ያብራራሉ፡፡ ‹‹የውጪ ባንኮች ቢመጡ ዝም ብለው አያበድሩም፡፡ካበደሩም በኋላ ይከታተላሉ፡፡የኛም ባንኮች በባንክ ህጉ መሰረት ይህን የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡ ››ሲሉ ያስገነዝባሉ፡፡ አቶ ክቡር ባለፉት ዓመታት ንግዱን ስርዓት ለማስያዝ በሚል ከወጡ ህጎች አብዛኛዎቹ ከፍተኛ ዋጋ የሚያስከፍሉ መሆናቸውንና መስተካከል እንዳለባቸው ይናገራሉ፡፡ አዋጭ በሆነ መንገድ ሰው ወደ ሥራ የሚመልስበትን ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ ያስገነዝባሉ፡፡ ባለፉት ዓመታት ምንም እንኳ ገና ሥራ ላይ ባይውሉም ከደንብና መመሪያዎች አንጻር አሰራሮችን ለማቅለል እየተሞከረ መሆኑን ጠቅሰው፣እንደዚያ ሲሆን ወጣቱን ወደ ሥራ ማስገባት እንደሚቻል፡፡ በቀጣይም የንግድ ማህበረሰቡን ለማሳደግና ንግዱን ለማጠናከር ብዙ መሰራት እንደሚኖርበት ያመለክታሉ፡፡አዲስ ዘመን ሀምሌ 16/2011 ኃይሉ ሣህለድንግል", "passage_id": "88d8e38e1600f1f76a4a59920b0df32a" }, { "passage": "የገንዘብ ሚኒስቴር የአስር ወራት አፈጻጸሙን በትናንትናው ዕለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ሪፖርቱን ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ባለፉት አስር ወራት የኢኮኖሚ ሚዛኑን በመጠበቅ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመፍጠር ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም የመንግስትን ወጪ በገቢው እንዲሸፍንና የዕዳ ጫናን ለማቃለል የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ የአገር ውስጥ መደበኛ ገቢ አፈጻጸምን በተመለከተ በ2011 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከታቀደው የፌዴራል መንግስት መደበኛ ገቢ 235 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ውስጥ በአስር ወራት መሰብሰብ የተቻለው 160 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ነው፡፡ አፈጻጸሙ የዕቅዱ 68 በመቶ በመሆኑ አፈጻጸሙን ለማሻሻል በግብረ ኃይሉ አመራር ሰጭነት ባለፉት አስር ወራት ውስጥ በርካታ የታክስ ህግ ማሻሻያ ጥናቶች መከናወኑን አስታውቀዋል፡፡ በጥናቶቹ ውጤት ላይ በመመስረት ስምንት መመሪያዎችና ሦስት ረቂቅ ህጎች ተዘጋጅተዋል። ከዚህም ባሻገር በሥራ ላይ ያለው የታክስ ቀረጥ ማበረታቻ ሥርዓት ያስገኘውን ጥቅምና ጉዳት ለመለየት የሚያስችል ጥናት ተካሂዶ አሰራሩን ወጥ ለማድረግ የሚያግዝ የህግ ረቂቅ የተዘጋጀ ሲሆን በማሻሻያዎቹ አማካኝነት በቀጣይ ከሃያ እስከ ሰላሳ ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት መታቀዱን ነግረዋል፡፡ የተረጋጋ የዋጋ ዕድገት እንዲኖር ባለፉት አስር ወራት ውስጥ መንግስት ጥብቅ የፊስካል ፖሊሲ ተግባራዊ ሲያደረግ መቆየቱንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ በዚህም የመንግስት ወጪ በገቢው እንዲሸፈን፣ የበጀት ጉድለቱም በዕቅድ ከተያዘው በላይ እንዳይንር የውጭ ብድር ጫናን የሚያረግቡ ተግባራትን በማከናወንና እንዲሁም የወጪ ጫና የሚፈጥሩ አዳዲስ ፕሮጀክቶች እንዳይኖሩና የተጀመሩትም የሚጠናቀቁበትን መንገድ የመንግስት ወጪ በዋጋ ንረት ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ ለመቀነስ ጥረት ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ የዋጋ ንረቱን በአንድ አሃዝ እንዲገደብ ለማድረግ አለመቻሉን ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት፡፡ በማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ መሰረት በአሁኑ ሰዓት አገራዊ አጠቃላይ የፍጆታ ዕቃዎች የዋጋ ዕድገት 12 ነጥብ 6 በመቶ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አህመድ፤ በዝቅተኛ የሁለት አሃዝ እንዲረጋጋ የተሰሩ ሥራዎች ግን ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በአብዛኛው በብድርና በእርዳታ የሚካሄዱ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ወቅታቸውን ጠብቀው በተያዘላቸው ጊዜ የማይጠናቀቁ በመሆናቸው መንግስትን ለተጨማሪ ወጪ እየዳረጉ መሆናቸውንም ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው አመላክተዋል። በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኩልም የክትትልና ግምገማ ችግር መኖሩን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ በመሆኑም በዘርፉ ያለውን ክፍተት ለማሻሻል ባለፉት አስር ወራት የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም በበጀት ዓመቱ የፕሮጀክቶችን ፕሮፋይል የማዘጋጀትና ችግር ያለባቸውን ፕሮጀክቶች የመለየት ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ ከዚህ አኳያ የ2010 የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም መነሻ በማድረግ የካፒታል ፕሮጀክቶች ፕሮፋይል ተገምግሞ የማጠቃለያ ሪፖርት የተዘጋጀ ሲሆን በ102 የፌዴራል መንግስት መስሪያ ቤቶች ከአንድ ሺ በላይ የሆኑ ፕሮጀክቶች ፕሮፋይላቸው ተገምግሟል፡፡ በተረደገው ግምገማም ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ ባለመጠናቀቃቸውና ከመጠን በላይ በመጓተታቸው መንግስት ከ 43 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ወጪ እንደሚያስወጣ አረጋግጠዋል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ፕሮጀክቶቹ በአመዛኙ የአዋጭነት ጥናት ሳይደረግባቸው ወደ ሥራ በመገባቱና አንዳንዶቹም ትክክለኛ ፕሮጀክት አዘገጃጀት ሥርአት ባለመከተላቸው በታቀደላቸው ጊዜ መጠናቀቅ ባለመቻላቸው መሆኑን ለመረዳት መቻሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ አዲስ ዘመን ግንቦት 29/2011", "passage_id": "29feec40a3cd2cd02ebdf40eb0dba8b7" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአስር አመቱ የልማት መሪ እቅድ አካታችና ጥራት ያለው ምጣኔ ሃብት እድገት፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ተቋማት እድገት፣ የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታና የዲጂታል ኢኮኖሚ እድገት ምሰሶዎችን ያካተተ ነው  ሲሉ የብሔራዊ ፕላንና ልማት እቅድ ኮሚሽነር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ።የብሔራዊ  ልማትና እቅድ ኮሚሽነሯ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በፖሊሲ ማተር ቆይታ አድርገዋል።በቆይታቸው  ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች እድገት ብታስመዘግብም የተመዘገቡት ለውጦች ግን እያንዳንዱ ዜጋን ተደራሽ ያደረጉ ባለመሆናቸው  በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ የዴሞክራሲና የተጠቃሚነት ጥያቄዎች ማስነሳቱን ገልጸዋል።በዚህም እያደገ ያለው ኢኮኖሚ  ሁሉን አካታች እንዲሆንና የተጠቃሚነት ጥያቄዎችን ለመመለስ የለውጥ ስራ መስራት አስፈልጓል ነው ያሉት።አሁን እየተከናወነ ያለው የአስር አመት መሪ እቅድም ድህነትን በግመሽ በመቀነስ ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ ካለቸው አገራት ተርታ ለማሰለፍ ያለመ ነው ሲሉ ገልጸዋል።ፖሊሲው የስራ አጥ ቁጥርን 9 በመቶ ለማድረስ እንደሚሰራና በመሰረተ ልማት  ዘርፍም ሰፊ ተግባራት እንደሚከናወኑ አስታውቀው÷ ለአብነትም በሃይል ልማት ዘርፍ በከተማና በገጠር 20 ጊጋ ዋት ሃይል ለማመንጨት መታቀዱን ጠቁመዋል።በማህበራዊ ዘርፉ ደግሞ በጤና፣ በትምህርትና በአቅም ግንባታ ተግባራት ላይ ፖሊሲው እንደሚያተኩርና ሌሎችንም ግቦች ያካተተ ነው ብለዋል።ይህንን ለማሳካት መሪ እቅዱ ሰፊ ምሰሶዎችን መያዙን ጠቁመው አካታች እና ቁልፍ ጥራት ያለው የምጣኔ ሃብት እድገት፣ የተናጠል ግብና ምርታማነት፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ተቋማት እድገት፣ የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታና ዲጂታል ኢኮኖሚ እድገት መካተቱን አስረድተዋል።የግል ሴክቴሩን ከፊት ቀዳሚ ማድረግ፣ አረንጓዴ ልማት፣ ተቋማዊ ግንባታ እንዲሁም የፍትህና ህዝባዊ አገልግሎት ማግኘት፣ ማህበራዊ አካታችነትና ማብቃት፣ በቀጠናው አካባቢ ልማትና ትስስር መፍጠር እንዲሁም  የጸጥታና ደህንነት ግንባታ ምሶሶዎችን መሪ እቅዱ ማካተቱን ነው የገለጹት።የመንግሰት እቅድ ብቻ ሳይሆን ህዝቡንና ባለ ድርሻ አካላትን እንዳካተተ የገለጹት ዶክተር ፍጹም ÷ ቀድሞ ተሰርቶ የሚሰጥ ሳይሆን ተቋማትና በላድርሻ አከላት ራሳቸው የሚያዘጋጁት ነው ብለዋል።መሪ እቅዱ ከ100 በላይ ከፍተኛ አማካሪዎች ጋር በመሆን መዘጋጀቱን ገልጸው÷ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ውጤትን መሰረት ያደረገ ምዘናን በስሩ ያካተተ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን! ", "passage_id": "96b0879c018a60b91105b613d026bf5e" }, { "passage": "በተያዘው ዓመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የታንዛንያ፣ አይቮሪኮስት እና ሴኔጋልን አስከትሎ በተያዘው ዓመት ከአፍሪካ ቀዳሚ እንደሚሆን የዓለም ባንክ ትንበያ   አመለከተ፡፡የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት 8 ነጥብ 3፣ ታንዛንያ 7 ነጥብ 2፣ አይቮሪኮስት 6 ነጥብ 8 እንዲሁም የሴኔጋል 6 ነጥብ 7 በመቶ ዕድገት እንደሚያስመዘግቡ የዓለም አቀፉ የኢኮኖሚክ ትንበያ በያዝነው ወር ላይ ባወጣው ትንበያ አመልክቷል፡፡እንደዓለም ባንክ ገለጻ ፤አገራቱ በመሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት፣ የግብርና ምርት ዕድገትና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መስፋፋት ለተመዘገበው ዕድገት ዓይነተኛ ምክንያት ተደርገው ተወስደዋል፡፡ አብዛኞቹ የአፍሪካ አገራት በተያዘው ዓመት 2 ነጥብ 6 እንዲሁም በቀጣዩ ዓመት 3 ነጥብ 2 ኢኮኖሚያዊ እድገት እነደሚኖራቸው ባንኩ ጠቁሟል፡፡ አነስተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸው አገራትና የምስራቅ አፍሪካ አገራት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ ስጋት እንደሚኖራቸው አመልክቷል ፡፡በተጨማሪም በምስራቅ አፍሪካ አገራት እየተከሰተ ያለው ድርቅ ምርታማነትን በመቀነስ፣ የምግብ ዋጋ በማናር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እክል እንደሚሆን ነው የገለጸው ፡፡በተመሳሳይ ሁኔታም ኢትዮጵያ የኬንያን የኢኮኖሚ ዕድገት በመብለጥ የአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት ቁንጮ ላይ እንደምትገኝ አይ ኤም ኤፍ በሚያዚያ ወር 2009 ዓመተ ምህረት ባወጣው መረጃ መገለጹን ጠቅሷል ፡፡በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የኢኮኖሚ የ29 ሚሊየን ዶላር ያህል ልዩነት እንዳለው በመጥቀስ ፡፡የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ከኬንው በእጥፍ ያህል የሚበልጥ በመሆኑ ለኢኮኖሚያው ዕድገት ልዩነቱ አዎንታዊ አስተዋፅኦ እንደዳለው ባንኩ አስረድቷል፡፡የኢትዮጵያ ሀገር ውስጥ ባለሀብቶች በመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው ንቁ ተሳትፎና የውጭ ባለሐብቶች በዋናነትም የቻይና ባለሐብቶች በሀገሪቱን ለኢንቨስትመንት ተመራጭ መዳረሻ ማድረጋቸው ኢትዮጵያ በኢኮኖሚያዊ ዕድገት ላይ የመሪነት ደረጃ ላይ እንድትቆናጠጥ ከተጠቀሱት ምክንያቶች ውስጥ መሆኑን ነው የተመለከተው ፡፡ –ትርጉም:- በሰለሞን ዓይንሸት ", "passage_id": "114bb1b253d64555b89149a93d526f61" } ]
b41ab3df7ddfdba00d7afd0b82e36d68
4cf7869a2b4b5931b73896dd61351cca
የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ህዝብና አገርን ያማከለ ሳይሆን በፖለቲከኞች ፍላጎት ላይ የተንጠለጠለ እንደነበር ተገለጸ
ዋቅሹም ፍቃዱ አዲስ አበባ፡- ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ህዝብና አገርን ያማከለ ሳይሆን አገሪቱን ሲመሩ የቆዩት ግለሰቦችና በሚያራምዱት ፖለተካ ላይ ብቻ የተንጠለጠለ እንደነበር ዶክተር ዲማ ነገዎ ተናገሩ። ዶክተር ዲማ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ የአገርና ህዝብን ፍላጎት ያማከለ ባለመሆኑ አገሪቱ በውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ስኬታማ አልነበረችም። ምክንያቱም በጊዜዉ የነበሩት የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ የአገርና ህዝብን ሳይሆን የገዥዉ ቡድን ጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ሲያስጠብቁ የነበሩ ከመሆናቸውም በላይ፤ ግለሰቦች ከስልጣን ሲወርዱ አብረዉ የሚጠፉ እንጂ አልፈዉ ህዝብና አገርን የሚጠቅሙ አልነበሩም። እንደ ዶክተር ዲማ ገለጻ፤ ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛችና የጥቁር ህዝቦች ተምሳሌት ብትሆንም፤ በተለያዩ ምክንያቶች ኢትዮጵያን ሊገፉ የሚፈልጉ እና ኩርፊያ ውስጥ ያሉ አንዳንድ አገሮችም አሉ። ከዚህ አንጻር ከቅርብም ከሩቅም በተለያዩ ምክንያቶች በብዙ ጠላቶች ከበባ ዉስጥ መሆኗን መረዳት ይቻላል። እነዚህ አገራት ደግሞ የፖለቲካ አኩራፊዎችን በማስታጠቅ ኢትዮጵያን ለማተራመስ ሲሠሩ ታይተዋል። ኢትዮጵያ ከድሮም ጀምራ ከፍተኛ የዉጭ ተጽዕኖ ሲደረግባት የነበረች መሆኗን የሚናገሩት ዶክተር ዲማ፤ በዚህ ረገድ በተለይ ከሱዳንና ግብፅ ጋር በጋራ ተጠቃሚነት፣ በዘላቂ ልማትና ሰላም ዙሪያ የተሠራዉ ሥራ ዝቅተኛ መሆኑን ያሚያሳዩ ክስተቶች መኖራቸውን ገልጸዋል። ለዚህ ጉልህ ማሳያ የሚሆነው ደግሞ የህዳሴው ግድብ መሆኑን በመጠቆምም፤ በዚህ ረገድ ግብፅ የዓባይ ጉዳይ በፊትአውራሪነት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሥራ እዉን እንዳይሆን ከአህጉር እስከ ዓለም አቀፍ መድረክ ያደረገችዉ ግፊት ቀላል እንዳልነበረ ይገልጻሉ። በሱዳን በኩልም ቢሆን የሚዋዠቅ አቋም እንደነበር እና ሀያላን አገራት ሳይቀር በግድቡ ዙሪያ የሚያሳዩት አቋም ለአንድ ወገን ያደላ መሆኑን የሚናገሩት ዶክተር ዲማ፤ በኢትዮጵያ በኩል ባለፉት ሁለት ዓመታት በዚህ በኩል የተሠራው ሥራ መልካም ቢሆንም አጥጋቢ እንዳልነበር ግን አልሸሸጉም። እንደ ዶክተር ዲማ አባባል፤ አሁን ላይ በትኩረት መሥራት ከተቻለ ኢትዮጵያ ጠንካራ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ኖሯት ተጽዕኖ ፈጣሪ እንድትሆን የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች አሏት። ለዚህ ደግሞ ገለልተኛ ተቋማትን የመገንባት ሥራ ማጠናከር፤ እንዲሁም ነፃ እና ፍትሐዊ የምርጫ ስርዓት እንዲኖር መሠራት አለበት። የህዳሴ ግድቡ ሲጠናቀቅም ከኢኮኖሚ ፋይዳ ባሻገር በፖለቲካውም ሆነ በውጭ ግንኙነቱ ረገድ የሚያሳድረው አዎንታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ በትብብር ዳር ማድረስ ያስፈልጋል። በተመሳሳይ ኢትዮጵያ ያላትን መልካም ገጽታ በማጉላት የሚታወቀው የመከላከያ ኃይሉን ተጠቅሞም ኢትዮጵያን በየትኛዉም የዓለም ክፍል የፀጥታ ማስከበር ላይ ማሳተፍ የሚያስችላት የወታደራዊ አቅም ለማጎልበት በበለጠ መሥራት ያስፈልጋል። ምክንያቱም መከላከያ ሠራዊቱ በዚህ መልኩ ሲሠራ ከሰላም ማስከበሩ ጎን ለጎን ለአገሩ አምባሳደር ሆኖ ይሠራል። በዚህ መልኩ ኢትዮጵያን ከውጭ አገራት ጋር ያላትን ግንኙት ዘላቂ ጥቅሟን በሚያስከብር መልኩ ጠንካራ ሥራ መሠራት እንዳለበት የጠቆሙት ዶክተር ዲማ፤ ከዚህ ጎን ለጎን የዉጭ ግንኙነቱ በአመዛኙ በዉጭ ቋንቋ የሚከወን በመሆኑ ለዉጭ ቋንቋዎች ትኩረት በመስጠት የቋንቋ አቅሙ ከፍ ያለ የሰው ኃይል በብዛትና በጥራት ማፍራት ላይ በትጋት ሊሠራ እንደሚገባም ምክረ ሃሳብ ለግሰዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37628
[ { "passage": " የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተጠናከረ የፓርላማ ዲፕሎማሲ አገራዊ ጥቅሞችን ከማስጠበቅ ባሻገር የገጽታ ግንባታ ሥራ እየሰራ መሆኑን የምክር ቤቱ አፈ-ጉባዔ አባ ዱላ ገመዳ ገለጹ። አፈ-ጉባዔ አባ ዱላ ገመዳ በተለይ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ምክር ቤቱ ከ28 አገራት ጋር የፓርላማ ወዳጅነት ቡድን በመመስረት የተሳካ የዲፕሎማሲ ሥራ እየሰራ ይገኛል።ምክር ቤቱ በተለያዩ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የፓርላማ መድረኮች ላይ በመሳተፍ ኢትዮጵያ ከመስራችነት አልፋ የአመራር ሚናዋን እንድትወጣ በማድረግ ላይ ነው።በዚህም ብሔራዊ ጥቅሟን በማስጠበቅ የአገሪቱን በጎ ገጽታ መገንባት መቻሉን ነው አፈ ጉባኤ አባዱላ የገለጹት።ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላት ተቀባይነት የሚወሰነው በአገር ውስጥ በሚካሄደው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ጥንካሬ ቢሆንም የአፍሪካን ጥቅም በተመለከተ በምትይዘውና በምታራምደው አቋም ተደማጭነቷ ከፍ እያለ መምጣቱን ጠቁመዋል።ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ከፍተኛ ተሳትፎ ባላቸው አገራት ላይ ትኩረት በማድረግ ውጤታማ የፓርላማ ዲፕሎማሲ ሥራ እያከናወነ ይገኛል።በተለይ የሌሎች አገራት ምክር ቤቶች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ በሚገባ ተገንዝበው ድጋፍ እንዲያደርጉ የፓርማ ዲፕሎማሲ ቁልፍ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።በዓባይ ወንዝ ፍትሃዊ አጠቃቀም ዙሪያ በኡጋንዳ የተደረሰውን ስምምነት አብዛኛዎቹ የተፋሰሱ አገራት ፈርመው መቀበላቸውን አፈ ጉባዔ አባ ዱላ አውስተዋል።ከዚህ አኳያ ምክር ቤቱ የፓርላማ የወዳጅነት ቡድን አጋሮቹ ስምምነቱን በየአገሮቻቸው ምክር ቤቶች ሲቀርብ እንዲያጸድቁት በፓርላማ ዲፕሎማሲ በኩል አስፈላጊውን መረጃ በመስጠት የሚጠበቅበትን ሥራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።በተለይ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ሲታዩ የነበሩ ብዥታዎች ላይ ምክር ቤቱ የማጥራት ሥራ ሲሰራ እንደቆየ ነው አፈ-ጉባዔው ያስታወቁት።ኢትዮጵያ በምታካሂዳቸው የማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች አገሮች በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው በማድረግ ጠንካራ ድጋፍ እንድታገኝ የሚደረግባቸው መድረኮች ናቸው።የፓርላማ ዲፕሎማሲ ከኢትዮጵያ ቀደም ብለው ሥርዓቱን ከዘረጉት አገራት በቂ ልምድ ለማግኘት እገዛ አድርጓል ብለዋል።በአንጻሩ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለውን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሌሎች እንዲረዱትና ከኢትዮጵያ እንዲማሩ ለማድረግም ዕድል ፈጥሯል።በዚህም ሕገ-መንግሥቱን መሰረት በማድረግ በአገሪቱ እየተገነባ ያለው የፓርላማ ዲፕሎማሲ ውጤታማ መሆን ችሏል።ኢትዮጵያ የዳበረ ዴሞክራሲ ካላቸው አገሮች ተሞክሮ ለመውሰድ እንደምታደርገው ሁሉ ከኢትዮጵያ ትምህርት የሚወስዱ በርካታ አገራት መኖራቸውን ጠቁመው ለአብነትም ሊቢያን ጠቅሰዋል።ኢትዮጵያ የበርካታ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች መኖሪያ እንዲሁም የተለያዩ ኃይማኖቶች ተቻችለው በጋራ የሚኖሩባት አገር ናት ያሉት አቶ አባ ዱላ እንዲያም ሆኖ የተረጋጋ ሠላም፣ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው ዕድገት ከማረጋገጥ ባሻገር ለአካባቢው ሠላም አስተዋጽኦ ማድረግ የቻለች አገር ነች።ይህን በሚገባ የተገነዘቡ የተለያዩ አገራትም የኢትዮጵያን ልምድ በተለያየ መንገድ ለመጋራት በሯን እያንኳኩ እንደሆነ ገልጸዋል።በቅርቡም በምክትል አፈ ጉባኤ የተመራ የሊቢያ የፓርላማ ቡድን በሽግግር ላይ የምትገኘውን አገራቸውን ወደ ህገ መንግሥታዊና ሠላማዊ ምዕራፍ ለማሸጋገር ከኢትዮጵያ ዝርዝር ልምድ ወስዷል።የፓርላማ ዲፕሎማሲ አገሮች በውጭ ጉዳይ ፖሊሲያቸው ላይ ተመስርተው በአስፈፃሚው የመንግሥት አካል የሚያደርጉት የአገር ለአገር ግንኙነት በሕዝብ ተወካዩ በኩል የሚደገፍበት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት በመባል የሚታወቅ የዲፕሎማሲ አካል ነው።ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የፓርላማ ሕብረት ቀደምት አባል ከመሆኗ ባሻገር በአንድ ወቅት ኅብረቱን በፕሬዝዳንትነት መምራት መቻሏን አውስተዋል።በአሁኑ ወቅትም የፓን አፍሪካ ፓርላማን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እየመራች ሲሆን የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት /ኢጋድ/ የፓርላማ ኅብረትንም በፕሬዝዳንትነት እየመራች ትገኛለች።ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ኅዳር ወር ላይ ከ87 በላይ አገራት ተሳታፊ የሆኑበት የአፍሪካ፣ ካሪቢያን/ፓስፊክና አውሮፓ ኅብረት ጥምር የፓርላማ ጉባዔን በብቃት ማስተናገዷ የሚታወስ ነው ። (ኢዜአ)", "passage_id": "ac6383deb9d4107ca1b8f39ab2ed7622" }, { "passage": "ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሃገራት ጋር ያላት ዲፕሎማሲ ጥብቅ አፍሪካዊ መሠረት የያዘ ነው\n\nየውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብያት ጌታቸው ዛሬ ጥር 8 ቀን 2012 ዓም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለሃገር ውስጥ እና ለውጭ ሚዲያዎች ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል።\nበመግለጫቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በጊኒ ሪፐብሊክ፣ በኢኳቶሪያል ጊኒ እና በደቡብ አፍሪካ ያደረጓቸውን ጉብኝቶች፣ በቀጣይ በአዲስ አበባ የሚካሄደውን የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ፣ 26ኛው የኢትዮ-ጅቡቲ የጠረፍ አስተዳደሮች ኮሚቴ ስብሰባ፣ የኢትዮጵያ እና ቻይና 50ኛ ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል አከባበር ዝግጅትን እና የኢትዮጵያ፣ የግብፅና የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቸ የዋሽንግተን ዲሲ ውይይት እና የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲን የተመለከቱ ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡\nኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሃገራት ጋር የምታራምደው ዲፕሎማሲ ጥብቅ አፍሪካዊ መሠረት የያዘ መሆኑን የገለጹትአቶ ነብያት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ3ቱ የአፍሪካ ሃገራት መንግስታት ግብዣ እ.ኤ.አ ከጥር 8 – 12/2020 ያደረጉት ይፋዊ የስራ ጉብኝት የተሳካ ነበር ያሉት አቶ ነብያት የሃገራቱን ግንኙነት ማጠናከር የተቻለበት፣ ከዚህ በፊት የተፈረሙ ስምምነቶች ተግባራዊ እንዲሆኑ ውሳኔዎች የተላለፉበት፣ አዳዲስ ስምምነቶች የተፈረሙበት እንዲሁም በየአገራቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች መብታቸው እና ደህንነታቸው ተጠብቆ የሚኖሩበት ሁኔታ የተመቻቸበት ነበር ብለዋል፡፡\nበተለይም የደቡብ አፍሪካው ጉብኝት የሃገራቱ ግንኙነት ወደ ስልታዊ አጋርነት ያደገበት እና በደቡብ አፍሪካ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ችግር መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት የተደረገበት ነበር፡፡ የኢትዮጵያውን መብቶች ልዩ ትኩረት እንዲያገኙ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሲሪይል ራማፎዛ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው የሚመራ ኮሚቴ አዋቅረው እርምጃ እንደሚወስዱም ቃል ገብተዋል፡፡\nጤናን፣ ቱሪዝምን እና የዲፕሎማቲክ እንዲሁም የሰርቪስ ፓስፖርት ባለቤቶች የያዙ የሃራቱን ዜጎች ያለ ቪዛ እንቅስቃሴን አስመልክቶም ሶስት የመግባቢያ ሰነዶች ተፈራርመዋል፡፡\nእ.ኤ.አ ከየካቲት 6-10/2020 በአዲስ አበባ የሚካሄደውን 33ኛው መደበኛ የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 36ኛው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ አስመልክቶም ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው፡፡አጠቃላይ ስብሰባውን የሚመራ ብሄራዊ እና ሌሎች ንዑሳን ኮሚቴዎች በየደረጃው ተቋቁመው ወደ ስራ መገባቱንም አቶ ነብያት ተናግረዋል፡፡\nበየ6 ወሩ የሚካሄደው 26ኛው የኢትዮ-ጅቡቲ የጠረፍ አስተዳደሮች ኮሚቴ ስብሰባም በጅግጅጋ ከጥር 14-16/2020 ተካዷል፡፡ በስብሰባውም የድንበር ደህንነትን፣ የፀጥታ አስከባሪ አካላት ትብብርን እና ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን መግታትን እንዲሁም በሁለቱ ሃገራት የሚካሄድ የትራንስፖርት እንቅስቃሴን በማሳለጥና በመሰል ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡\n\nኢትዮጵያ እና ቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የመሰረቱበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነውም ብለዋል ቃል አቀባዩ፡፡\nከ1970 ጀምሮ የተመሰረተው የሃገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በፈርጀ ብዙ ዘርፎች እያደገና እየተጠናከረ መጥቶ እ.ኤ.አ በ2017 ወደ ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂያዊ ትብብር ደረጃ ከፍ ብሏል፡፡\nየኢትዮጵያ፣ የግብፅና የሱዳን የውጭ ጉዳይ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች እ.ኤ.አ ከጥር 13-15/2020 ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የአሜሪካ የግምጃ ቤት ሚኒስትር ቢሮ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሌት እና ውሃ አለቃቀቅ ላይ ያካሄዷቸውን የቴክኒክ ምክክሮች በተመለከተ የአሜሪካና የዓለም ባንክ ተወካዮች በታዛቢነት በተገኙበት ተወያይተዋል፡፡\nሚኒስትሮቹ አስቀድመው ባካሄዷቸው የቴክኒክ ስብሰባዎች ላይ በተነሱ ነጥቦች ውይይት ካካሄዱ በኋላ እስከ ጥር 28 ቀን 2020 ድረስ የቴክኒክ ውይይቶች እንዲቀጥሉ እና ውጤቱ እንዲቀርብ መስማማታቸን፤ በቀጣይ የቴክኒክ ውይይት እልባት ያገኛሉ ተብለው የሚጠበቁት የውሃ ሙሊት እና አለቃቀቅ ስርዓት የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ መግባባት እንዲጠናቀቅ እንደሚሰራ አብራርተዋል።\nከዜጋ-ተኮር ዲፕሎማሲ አንጻር ከጥር 6 እስከ 11 ቀን 2012 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ቀናት ውስጥ 238 ኢትዮጵያዊያን ከሌባኖስ ወደ ሀገራቸው እንደሚገቡ አቶ ነብያት ገልጸዋል።\n", "passage_id": "ae72bbb8d788bc274cca0f36c4574d36" }, { "passage": "የኢፌዴሪ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያን ውጪ ግንኙነት ብሄራዊ ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ እንዲመራ የሚያስችል አላማ አስቀምጦ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ገለጸ ፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአዲሱ ሪፎርም ተመሥረቶ የመደባቸውን አምባሳደሮችና ሚሲዮነሮች አቅምን ለማጎልብት የሚረዳ ሥልጠና ለአሥር ቀናት የሚቆይ ሥልጠና አዘጋጅቷል፡፡ሥልጠናው ከዛሬ የሚጀምር ሲሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገብየሁ  ተገኝተው ሥልጠናውን አስጀምረውታል ።በሥልጠነው ማስጀመሪያ ስነስረዓት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ሚኒስትሩ ዶ/ር ወርቅነህ ገብየው እንደተናገሩት ሠልጣኖቹ በተመደቡብት ሀገር የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ማስቀደምና ዜጎቻቸውን ማገልገል ቅድሚያ ሊሠጡት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል፡፡የሀገራት ግንኙነት በዋናነት የሚመሰረተው በዲፖሎማሲያዊ ስኬት መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ እውቀትን፤የሰው ሀይልንና ዘመኑ ያፈራቸውን ዲጂታል መሳሪያዎች በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ ስራ ከፊታቸው እንደሚጠብቃቸውም አንስተዋል፡፡ለየት ባለ መልኩም ሥራውን ማገዝ እንዲችሉ የትዳር አጋሮቻቸው በስልጠናው በመጨረሻ እንዲካተቱ ተደርጓል ብለዋል፡፡በስልጠናው 20 አምባሳደሮችና ሁለት ሚሲዮነሮች የተካተቱ ሲሆን ከውጪ ግንኙነት አካላትና ከተለያዩ ተቋማት በተውጣጡ አሰልጣኞች በተዘጋጁ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ቆይታ እንደሚኖራቸው ማወቅ ተችሏል፡፡", "passage_id": "f3f34aca4baba2470015320719cb4c2b" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 26 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሁኑ ወቅት የአገርን ሉአላዊነትና የህዝብን ደህንነት ማረጋገጥ የመንግስት ቀዳሚው ጉዳይ መሆኑን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተናገሩ።ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት የአገርን ብሄራዊ ጥቅምና የህዝብን ህልውና ለውጭ ኃይል አሳልፎ መስጠት አግባብ አለመሆኑንም ጠቅሰዋል።የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን፣ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር አቶ ዛዲግ አብርሃ እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ በኮሮና ቫይረስና በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ውይይት አካሂደዋል።በአሁኑ ወቅት የአገርን ሉአላዊነትና የህዝብን ደህንነት የማረጋገጥ ጉዳይ የመንግስት ቀዳሚ ጉዳይ መሆኑን የተናገሩት ሃላፊዎቹ በተለይም የህዝቡን ጤንነት መጠበቅና የህዳሴው ግድብን ማጠናቀቅ ቅድሚያ የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት የአገርን ብሄራዊ ጥቅምና የህዝብን ህልውና ለውጭ ሃይል አሳልፎ መስጠት አግባብ አለመሆኑን ገልጸዋል።የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን መንግስት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል፣ የህዝቡን ደህንነት ለመጠበቅና የዴሞክራሲ ባህል እንዲዳብርና የአገርን ሉአላዊነት የማስጠበቅ ስራዎችን እየሰራ ለውጥም እየታየ ነው ብለዋል።“እኛ አጀንዳችን ህዝብ የማዳን” ነው ያሉት ሃላፊው፤ ታላቁን የህዳሴ ግድብ ግንባታ አጠናቆ  ውሃ በመሙላት  ሀገሪቱን ከችግርና ድህነት መውጫ መሳሪያ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አፈፃፀምም ሃይል የተሞላበት ሳይሆን የዴሞክራሲ ምህዳሩን የማይጫንና በህግ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ሊያስወቅስ አይገባም ሲሉም ተናግረዋል።በአሁኑ ወቅት ስለ ምርጫና ስለ ፖለቲካ የተለያዩ ሃሳቦች መነሳታቸው እንደ ሃሳብ ጤናማ ቢሆንም ከሃሳብ አልፈው የህዝብንና የአገርን ብሄራዊ ጥቅም የሚጎዱ መሆን የለባቸውም ብለዋል።“የኢትዮጵያ ህዝብ ብጥብጥና ግጭት ሰልችቶታል፣ይህንን ሃሳብ የሚቀበልበት ጊዜም አይደለም “ያሉት አቶ ንጉሱ፤ መንግስት የህዝብን ደህንነትና የአገርን ሉአላዊነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ችግሮችን እንደየመልካቸው ይመልሳል በማለት ነው የተናገሩት።በአሁኑ ወቅት ምርጫ እናካሂድ ማለት “አንተ እየሞትክ እኔ ልመረጥ ማለት ነው” ያሉት ደግሞ አቶ ዛዲግ አብርሃ ሲሆኑ ከሁሉም በፊት የህዝብ ደህንነትና የአገር ሉአላዊነት ይቀድማል ሲሉ ተናግረዋል።የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ በበኩላቸው የኮሮና ቫይረስ የሚያስከትለውን የጤና ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ጫና በመከላከል በኩል እስካሁን ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን ነአስረድተዋል።“ሰራተኛው ከስራ እንዳይፈናቀል፣ተቋማት እንዳይሞቱ እንደግፍ በሚል መንግስት የተቋማትን እዳ ፣የግብር እዳ ሰርዟል፣ተጨማሪ ፋይናንስ ወደ ኢኮኖሚ ውስጥ እንዲገባ አድርጓል፣ሰራተኞች እንዳይበተኑ የታክስ እፎይታ ተሰጥቷል” ነው ያሉት።እነዚህ ሁሉ ማሻሻያዎች  ኢኮኖሚው ብዙ ሳይጎዳ የበሽታውን ችግር ለማለፍ ያግዛል በማለት፤ ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉና የኮሮና ቫይረስ በሽታ በአጭር ጊዜ ከቆመ ኢኮኖሚው ብዙም ሳይጎዳ እንደገና አንሰራርቶ የእድገት መስመራችንን መቀጠል አንችላለን  ነው ያሉት ዶክተር እዮብ።መንግስት የኮሮና ቫይረስን ከመከላከል አኳያ ጥሩ ውጤት እያመጣ ቢሆንም የቫይረሱ ስርጭት በገጠሩ የአገሪቱ ክፍል መታየቱ የሚያስደነግጥ መሆኑንና ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎቹ አሳስበዋል።", "passage_id": "21b6a16e5dea12f47f30c1edeaa283ae" }, { "passage": "የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በኤርትራ የሚያደርጉት ጉብኝት በአገራቱ መካከል ሰላም ለማምጣት ሚናው የጎላ መሆኑን ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ለሃያ ዓመታት የነበራትን “ሞት አልባ ጦርነት” ወደ ሰላም ለመቀየር እንቅስቃሴ መጀመራቸው ይታወሳል።ይህንንም እውን ለማድረግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት አስመራ መግባታቸውን የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን ለሁለቱ አገራት ሰላም በማምጣት ረገድ በአዎንታዊ መልኩ ተመልክተውታል።ሽፋን ከሠጡት መካከል ቢቢሲ፣ ሮይተርስ፣ አልጀዚራና ዋሺንግተን ፖስት ይገኙበታል።መገናኛ ብዙሃኑ በዘገባቸው “ከሃያ ዓመት በኋላ ኤርትራን በመጎብኘት የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ መሪ ሆኑ”  ሲሉም ተሰምተዋል።“የሁለቱ ተቀናቃኝ አገራት ታሪካዊ ግንኙነት” በማለት የገለጸው ሮይተርስ የዜና ወኪል ለሃያ ዓመታት በወታደራዊ ተጠንቀቅና በጥንቃቄ ሲተያዩ የነበሩት የሁለቱ አገራት መሪዎች ግንኙነት እጅግ ታሪካዊ መሆኑን አትቷል።ለጉብኝቱ የኤርትራ መንግሥት ከፍ ያለ ትኩረት ሰጥቶ ከሳምንት በፊት ደማቅ አቀባበል ለማድረግ ዝግጅት ሲያደረግ ቆይቷል ሲሉም በዘገባቸው ጠቅሰዋል።በርካታ ኤርትራውያንም ወደ አደባባይ ወጥተው ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ያላቸውን አክብሮት እንደገለጹና የኢትዮጵያና የኤርትራ ሰንደቅ አላማዎች ጎን ለጎን መውለብለባቸውን ጠቁመዋል።በጃፓን የኤርትራ አምባሳደር እስጢፋኖስ አፈወርቂን ጠቅሶ የዘገበው ቢቢሲም “አቀባበሉ በኤርትራ ታሪክ ለማንኛውም መሪ ያልተደረገ” መሆኑን ገልጿል።በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን ለተቀረው ዓለም ክፍት ለማድረግ ከፍተኛ ለውጥ ማድረጋቸውንም አክለዋል።በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጉዘው አስመራ ያረፉት ዶክተር አብይ ከአየር ማረፊያው እስከ ቤተ መንግስት በኤርትራውያን ታጅበው  መድረሳቸውንም እንዲሁ።ዋሺንግተን ፖስትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ለበርካታ ዓመታት ከአገራቸው ጋር በጠላትነት ከሚተያዩት ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ለመነጋገር ኤርትራ ገብተዋል ብሏል።በተመሳሳይ ኤርትራ ሲደርሱም ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር መተቃቀፋቸውንና በርካታ ህዝብ ወደ አደባባይ ወጥቶ እንደተቀበላቸውና በአደባበዮች ላይም የአገራቱ ሰንደቅ ዓላማም ጎን ለጎን መውለብለቡን ነው ያተተው።ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ የኤርትራ ግንኙነት በአዎንታዊ መልኩ መቀየሩም ጉዳዩን በሚከታተሉ በበርካታ ሰዎች ላይ አግራሞት መጫሩንም አንስቷል ዘገባው።ጠቅላይ ሚኒስትሩም ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የሚያደርጉት ውይይት በአገራቱ መካካል የነበረውን የቀድሞውን ሰላም ለማስመለስ ሚናው የጎላ መሆኑን አስታውሷል።አልጀዚራም በተመሳሳይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኤርትራ ጉብኝት ታሪካዊና አገራቱ ወደ ሰላም ለመመለስ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት አስፍሯል።በተለይም በፌስቡክ የተላለፉ አስተያየቶችን ጠቅሶም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የአገራቱን ሰላም በማረጋገጥ በህዝብ ዘንድ እጅግ ትልቅ ግምት የሚሠጠው መሆኑን አስረድቷል።እንዲያውም ከአዲስ አበባ በጉዳዩ ላይ ባለሙያም አነጋግሮ ” አገራቱ በጋራ ያላቸው ታሪክ በተናጠል ካላቸው ታሪክ ይልቃል ” ብሎ መናገሩን ጠቁመዋል።  አገራቱ የጋራ ታሪክ፣ ባህል፣ ኃይማኖትና በጋራ ችግሮችንም ማለፋቸውን እንዲሁም አገራቱ በማኅበራዊ፣ በምጣኔ ኃብትና በፖለቲካው ያላቸው አጋርነት ለቀጣንውም የሚጠቅም መሆኑን ዘገባው ባለሙያውን ጠቁሞ አስፍሯል። ጉብኝቱን ከነዚህ መገናኛ ብዙሃን በተጨማሪ የኤርትራ ቴሌቪዥን በቀጥታ ሲያስተላልፈው በኢትዮጵያ በኩልም በተለያዩ ሚዲያዎች ትልቅ ሽፋን ተሰጥቶታል።(ኢዜአ)", "passage_id": "747644900ed418bcdf99e32960769ef6" } ]
db801446f4e478a1029c23512b469e3b
73f3b79a04f40b29cb24b1527d8e65e5
ከትልቅ ድል የተገኘ ትልቅ ተስፋ
 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) በ2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ የምድባቸውን ሁለተኛ ፈተና እንደ ተራራ የገዘፈ የእግር ኳስ ስም ካላት ኮትዲቯር ጋር ባህርዳር ላይ ተፋልመው የሚፈልጉትን ውጤት አግኝተዋል። የተጋጣሚያቸው ክብደት ከተመዘገበው ድልና የጨዋታ የበላይነት አኳያ ዳግም የኢትዮጵያን የእግር ኳስ ትንሳዔ ከማነቃቃት ባለፈ በፖለቲካ ትኩሳት እየተሸረሸረ የመጣውን ብሔራዊ ስሜት የመጠገን ሃይል እንዳለው መታዘብ ይቻላል። ይህ ድል ኢትዮጵያ እንዳለፉት ዓመታት ወደ መሰረተችው የአፍሪካ ዋንጫ ለመመለስ ዳግም ሦስት አስርት ዓመታት እንደማትጠብቅ ጠቋሚም ነው። ያምሆኖ ይህ የተነቃቃ መንፈስ እንዳይከስም ሥጋት የለበትም ማለት አይደለም። የዋልያዎቹ አለቃ ኢንስትራክተር አብረሃም መብራቱ ‹‹ጨዋታውን እንደተመለከታችሁት በብዙ ብልጫ ኮትዲቯርን የበለጥነበትና በተሻለ የኳስ ቁጥጥር እንዲሁም የግብ ሙከራ ያሸነፍንበት ነው:: አምላክ ደግሞ ልፋታችንን ቆጥሮ ለድል አብቅቶናል:: ከሁሉም በላይ ቡድኑ ላይ እየታየ ያለው መሻሻል ጥሩ ነው:: በማሸነፍ ውስጥ የተፈጠሩትን ስህተቶችና የሚጎሉ ነገሮችን እያሟላን ጠንካራ ቡድን መገንባቱን እንቀጥላለን:: እግር ኳስ ሂደት ነው: ይሄን ጨዋታ ስላሸነፍን ሂደቱ አለቀ ማለት አይደለም:: ይሄ ድል ትልቅ የሞራል ስንቅ ይሆነናል›› በማለት ከጨዋታው በኋላ ለመገናኛ ብዙሃን አስተያየት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ጠንካራ ለማድረግ የውጭ ሀብት እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት አሰልጣኙ ‹‹ውጭ ያሉ ተጨዋቾቻችን ሀብቶቻችን ናቸውና በነሱ አጠቃቀም ላይ ጠንካራ ሥራ መሥራት ይኖርብናል። ምክንያቱም እነሱ የሚያገኙት ስልጠና: የሚገኙትን ኢንተርናሽናል ተጽዕኖና ፕሮፌሽናሊዝም አስተሳሰብ ለብሔራዊ ቡድናችን ይጠቅመናል:: ከዚህም ሌላው አገርን ወደው ለመምጣት መፈለጋቸው የበለጠ ብሔራዊ ቡድኑን ይገነዘባዋል የሚል ጠንካራ አሳብ አለኝ›› ብለዋል። አሰልጣኙ እንደገለፁት በውጭ አገራት ሊጎች የሚጫወቱ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ለቡድኑ ቀጣይ ጥንካሬ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱ አይቀርም። ከዚያ ባሻገር ግን ይህን የተለኮሰ መነቃቃት እንዳይቀዘቅዝ በተለይም ፌዴሬሽኑ በርካታ ሥራዎች እንደሚጠብቁት እውን ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች በተራራቀ ጊዜ መካሄዳቸው የተፈጠረውን መነቃቃት ሊያቀዘቅዙ ከሚችሉ ነጥቦች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ባሸነፉ ማግስት ሌሎች ጨዋታዎችን ቢያከናውኑ የተፈጠረው መነቃቃት ሳይቀዘቅዝ ሌላ ድል ለማስመዝገብ ላይቸገሩ ይችላሉ። ይሁን እንጂ ቀጣዩን የማጣሪያ ጨዋታ ከበርካታ ወራት በኋላ በዓመቱ መጨረሻና መጀመሪያ አካባቢ ማድረጋቸው አሁን የተፈጠረው መነቃቃት ላይ ውሃ ሊቸልስበት ይችላል። የቡድኑ ስብስብም ለረጅም ጊዜ ተለያይቶ ሲገናኝ አሁን ያለው የአሸናፊነት መንፈስና መነቃቃት በነበረበት ላይገኝ ይችላል። ይህን ሥጋት ግን ፌዴሬሽኑ ከወዲሁ ትኩረት ሰጥቶ ከተዘጋጀበት መቅረፍ እንደሚችል ይታመናል። በዋናነት ይህን ችግር ለመቅረፍ የወዳጅነት ጨዋታዎችን በፊፋና በካፍ መርሐ ግብር መሠረት ማከናወን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኖች በየትኛውም ደረጃ የወዳጅነት ጨዋታዎች ማድረግ የዘወትር ችግራቸው መሆኑ ይታወቃል። ይህን ክፍተት ፌዴሬሽኑ እየደፈነ መሄድ ከቻለና ቡድኑ ተደጋጋሚ የአቋም መለኪያና የወዳጅነት ጨዋታ ማግኘት ከቻለ አሁን ያለውን መነቃቃት ማስቀጠል ብቻም ሳይሆን የቡድኑ ውህደት ላይ ትልቅ ለውጥ መፍጠር እንደሚቻል ይታመናል። በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያው አሁን ላይ ማዳጋስካር በ2 ጨዋታ፣ በ6 ነጥብና በ5 ንፁ ግብ ዋልያዎቹ የሚገኙበትን ምድብ ትመራለች። ኢትዮጵያ በ2 ጨዋታ፣ በ3 ነጥብና በ0 ግብ ሁለተኛ ስትሆን ኮትዲቯር ከዋልያዎቹ ጋር በተመሳሳይ ነጥብና የግብ ልዩነት ትቀመጣለች። ኒጀር በ2 ጨዋታ በ0 ነጥብና በ5 የግብ ዕዳ መጨረሻ ላይ ትገኛለች። ይህ ዋልያዎቹን ከስምንት ዓመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ ለመመልከት በእጅ ያሚገኝ ትልቅ ዕድል ነው። የምድቡን ቀሪ ጨዋታዎችና ተጋጣሚዎች ከግምት በማስገባት ዋልያዎቹ አፍሪካ ዋንጫው ላይ ለመድረስ ያላቸውን ተስፋ ካሰላነው ወደ ተወዳጁ መድረክ ለመመለስ ከዚህ የተሻለ ዕድል እንደሌለ መገንዘብ ይቻላል። ቀጣይ የማጣሪያ ጨዋታዎች ከበርካታ ወራት በኋላ መካሄዳቸው አሁን የተፈጠረውን መነቃቃት እንዳያቀዘቅዙት ሥጋት እንደመፍጠሩ ሁሉ ዋልያዎቹ ያላቸው ቀሪ መርሐ ግብር ተስፋ የሚሰጥ ነው። ይህም በሜዳቸው የገነደሱት የምድቡ ሃያል ቡድን ኮትዲቯር ጋር የሚያደርጉት የመልስ ጨዋታ የማጣሪያው መጨረሻ መሆኑ ነው። ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ከመግጠማቸው አስቀድመው ከኒጄር ጋር የደርሶ መልስ ጨዋታ ያደርጋሉ። ከዚያም ማዳካስካርን በሜዳቸው ይገጥማሉ። በዚህ መርሐ ግብር መሰረት አሰልጣኝ አብረሃም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየገነቡት የሚሄዱት ቡድን እንዳሁኑ አዳዲስ ለውጦችን መፍጠር ከቻለ በሜዳዋ ሁለት ሽንፈቶችን ከቀመሰችውና የምድቡ ደካማ ቡድን ከያዘችው ኒጄር ጋር በሚኖሩት የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ቢያንስ አራት ነጥብ ማግኘት ከባድ አይሆንም። ዋልያዎቹ ኒጄርን በሜዳዋ ገጥመው አንድ ነጥብ ይዘው ከተመለሱ በሜዳቸው ሦስት ነጥብ መሰብሰብ ይሳናቸዋል ተብሎ አይጠበቅም። ቀጣይ ተጋጣሚ ማዳካስካር እንደመሆኗ ከዚህ ጨዋታም ቀላል ባይሆንም ሦስት ነጥብ መሰብሰብ የማይቻል ነገር አይደለም። ምክኒያቱም ማዳጋስካርን የሚገጥሙት እዚሁ በሜዳቸው ነው። ባለፈው ቅዳሜ ማዳጋስካር በሜዳዋ ዋልያዎቹን 1ለ0 ስታሸንፍ ያን ያህል ከባድ ቡድን እንዳልሆነች ታይቷል። ይህን ስሌት ዋልያዎቹ ማሳካት ከቻሉ የመጨረሻውን ማጣሪያ ከሜዳቸው ውጭ በኮትዲቯር ቢሸነፉ እንኳን ወደ ካሜሩን የሚወስዳቸውን ትኬት በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ ማለት ነው። በዚህ ስሌት መሰረት ነገሮች ሊጓዙ የማይችሉበት አጋጣሚ እንዳለ ሁሉ እንዳለፈው ጨዋታ ያልተጠበቁ ድሎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉም እውን ነው። ይህም ለዋልያዎቹ ቀጣይ የአፍሪካ ዋንጫ ጉዞ ትልቅ የሥነ ልቦና ስንቅ ሆኖ ያገለግላቸዋል። ይህን ተስፋ እንዳይከስም ግን የወዳጅነት ጨዋታዎችን ጉዳይ ከወዲሁ አጥብቆ መያዝ ለነገ የሚባል የቤት ሥራ አይሆንም። አዲስ ዘመን ኅዳር 11/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22892
[ { "passage": "ስመ ገናናዋ የዓድዋ መዝሙር እናት እጅጋየሁ ሽባባው እንዲህ የተቀኘችው በከንቱ አይደለም፡፡\n\nበኩራት፣በክብር፣በደስታ፣በፍቅር፣\n\nበድል እኖራለሁ ይኸው በቀን በቀን፤\n\nደግሞ መከራውን ያን ሁሉ ሰቀቀን፡፡\n\nይህ ድብልቅልቅ ስሜት፣ረቂቅ ትውስታ ሁለት ገጽታ ያለው የሁሌ ትዝታ፣ መዝሙርና ሙሾ ነው፡፡ በጦርነቱ ዕለት እንኳ ከዚያ አስደናቂ ድል በኋላ በዐጼ ምኒልክ፣በራስ መኮንንና ሌሎችም ጀግኖች ፊትና ልብ ላይ የሚንቀዋለል ስሜት ነበር፡፡ ከዚያ አስደናቂ ድል በኋላ የወደቁት እነ ፊታውራሪ ገበየሁ አባገራውን የመሳሰሉ ጀግኖች ሞት ለጓዶቻቸው ሕመም ነበር፡፡…ሰው ከፍሎ፣ውድን ሰጥቶ ሌላ ውድ ነገር መቀበል ቀላል አልነበረም!!\n\nጀግኖቻችን የዓለም ዕብሪተኛ በስላቅ ምላሱን አውጥቶ እንዳያላግጥብን፣ የተሳለልንን ቢላ ነጥቀው፣ ቀንበሩን ከጫንቃችን የሰበሩት በራሳቸው ደም ነው፤ የድል ዜና ያሰሙን፣ ገድሉን የፈጸሙትና በታሪካችን ላይ ዘውድ የደፉት ከጠላት ጋር ተናንቀው ደምና ላብ ከፍለው ነው፡፡ እናም ዛሬ ሲታሰቡን የማያረጁና በታሪካችን ገጾች የማይደበዝዙ ዝርግፍ ጌጦቻችን ሆነው ነው፤ ስለዚህ ሁሌም እንኮራባቸዋለን፡፡\n\nታዲያ ይህንን አንገት ቀና የሚያደርግ የነጻነት ተጋድሎ፣ ጭንጫ መሬት ላይ የወደቀ ዘር ሆኖ አልቀረም፡፡ ይልቅስ በከያኒዎቻችን ልብ በቅለውና አድገው፣ እሸት ሆነው፣ አብበው ፈክተዋል፤ በዜማ አጊጠው፣በጥበብ ተቀምመው፣ በልባችን በውብ ቀለም እንደ ጅረት ፈስሰዋል፡፡\n\nከነዚህ ድሉ ከወለዳቸው ከያንያን ውስጥ ስለ ዓድዋም ከፍ ባለ ጥበባዊ ቁመና፣ በሠፊ ምናብ ክንፍ ቅኝት የምናደንቃቸው ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህንና እጅጋየሁ ሽባባው፣ ሌሎችም ወጣት ከያንያን አባቶቻችንን ከዘከሩበት ስራ በጥቂቱ መዳሰስ የወቅቱ ጥያቄና የኔም የዚህ ጽሑፍ ዓቢይ ጉዳይ ነው፡፡ \n\nበርግጥም ከታሪክ አንጻር የዓድዋን ድል ያህል ግዙፍና ለማንጸሪያነት የሚበቃ ሰማይ ጠቀስ ታሪክ፣ አሻራ ያለው ድንቅ የማይዳሰስ ሀውልት የለንም፡፡ ዓድዋ ዓለም ዐቀፍ ግርማ ያገኘ፣የታሪክ ሰነዶችን ያጣበበ የዓለማችን ታላቅ ገድል ነው፡፡\n\nሰለዚህም በየስፍራው በየሀገሩ ብዙ ተጽፎለታል፤ ብዙ ተዘምሯል፡፡ እኛ ጋ ሲመጣም በያመቱ፣አንዳንዴም በያጋጣሚው በጥበብ ሰዎች ብዕር ይዘመራል፡፡ ከወጣቶቹ የሆሄ ስነጽሑፍ ሽልማት የግጥም ዘርፍ የአንደኛው ዙር ተሸላሚ የሆነው ወጣት አበረ አያሌው ‹‹ፍርድ እና እርድ›› በሚለው መጽሐፉ፣ ስለ ዓድዋ እንዲህ ያለው ለዐለም ዐቀፋዊነቱ ክብር ይመስለኛል፡፡\n\nአድዋ ሰፈር አይደለም-አድዋ መንደር አይደለም\n\nሀገር ነው ከነታሪኩ-አህጉር ነው፣ሰ……ፊ ዓለም፡፡\n\nእነምኒልክ ጦር ይዘው-ከመድፍ የተዋደቁ\n\nጎራዴ መዘው የሮጡ-በጠብ-መንጃ አፍ ያለቁ\n\n ለጓጉለት ነፃነት -ደማቸውን ያፈሰሱ\n\nለሰፈር ብቻ አይደለም-ያህጉር ድል አታንኳሱ፡፡ይላል፡፡\n\n ይህ ግዝፈቱን ማሳያ ነው፡፡ ዓድዋ በርግጥም ሩቅ፣ ለምናብም ልጥጥ ነው፡፡ ነግረው አይጨርሱትም፤ አፍሰው በጎተራ አያኖሩትም፡፡ እንደ ዋርካ ባለ ብዙ ቅርንጫፍ፣ በእልፍ ቃል የማይገለጥ፣ከአእምሮ በላይ ነው፡፡ የአንዲት ደሃ ሀገር የገበሬ ጦር ዘመናዊ ስልጠና የወሰደ የአውሮፓዊት ሀገር ጦር አሸነፈ ማለት እንደ ተረት የሚቆጠር ነው፡፡…ግን በእውኑ ዓለም እውን ሆኖ ዓለምን አደናግሯል፡፡\n\nስለዚህ የጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ችቦ፣ የአሸናፊነት ማሳያ ፊልም፣ የማይጠበቅ ተዐምር ብንለው ያስኬዳል፡፡!\n\nስመ ጥሩ ከያኒ ቴዎድሮስ ካሳሁንም ‹‹ጥቁር ሰው››ብሎ በሰየመው አልበም ስለ ምኒልክ ያቀነቀነው፣ ስለ ቀለሙ ሳይሆን ድንበር የለሽነቱን ለማሳየት ይመስለኛል፡፡ ዓድዋ ድንበር የሌለው ድል፣ ጥቁር ሕዝቦችን ከተኙበት ለነጻነት ያባነነ የማንቂያ ደወል ነው፡፡ \n\nበርግጥም ያለጥርጥር የዓድዋ ድል... ", "passage_id": "86fb41d90a9d5fccceaf50c44ba2fa1a" }, { "passage": "አፍሪካ በ 2017/18 የውድድር ዓመት በዓለም አቀፍ ይሁን በአህጉራዊ የስፖርት መድረክና ሁነቶች ስትታወስ ስኬትም ውድቀትንም አስተና ግዳለች። አሳዛኝ ታሪኮችንም አሳልፋለች። ከእነዚህ የውድድር ዓመቱ አብይት ሁነቶች መካከል ደግሞ የሚከተሉት ከሁሉ ልቀው ይታወሳሉ።አሳፋሪው የአፍሪካ የዓለም ዋንጫ የተሳትፎ ታሪክ\nአፍሪካውያኑ ኮከቦች ምንም እንኳን በተለያዩ ታላላቅ ሊጎች አገራቸውንና ስማቸው ከፍ አድርገው ማስጠራት ቢችሉም በአህጉር አቀፍ ውድድሮች በተለይ በታላቁ የዓለም ዋንጫ የሚያሳዩት አቋም ግን ብዙዎችን ግር ያሰኘ ነበር።በእርግጥ አፍሪካውያኑ ተጫዋች በዓለም ዋንጫው መድረክ መገኘት የሚያጎናፅፈውን ክብርና የሚሰጠውን የተለየ ስሜት ጠንቅቀው ቢያውቁትም ከተሳትፎ ባለፈ በመድረኩ ላይ አዲስ ታሪክ መስራት የምንጊዜም ህልምና ምኞታቸው ነው።ይሁንና ይህ መሻታቸው ዓለም ዋንጫው ከተጀመረ ዓመታትን ተሻግሮም ውጤት ማምጣትና በዋንጫ መታጀብ አልሆነለትም።ከወራት በፊት በተካሄደው 21ኛው የሩሲያ የዓለም ዋንጫ በሦስት የሰሜንና በሁለት የምዕራብ አፍሪካ አገራት የተወከለችው አፍሪካ፣ እግር ኳሳዊ የታሪኩ አሸናፊነት አቅጣጫን የመቀየር አቅም ያላቸው ተጫዋቾችን ይዛ ሞስኮ ብትደርስም የፈለገችውን ግን ማግኘት አልቻለችም።\nከዓለም ዋንጫ መጀመር አስቀድሞ በርካቶች በዓለማችን ታላላቅ ሊጎች ትልቅ ተፅዕኖ መፍጠር የቻሉና አገራቸውን ወክለው ሩሲያ ያቀኑ ኮከቦችን ዋቢ በማድረግ በዘንድሮው ፍልሚያ አፍሪካ የተሻለ ውጤት እንደሚኖራት ቢተነብዩም በሞስኮ ሰማይ ስር የሆነው ግን ከዚህ ፈፅሞ የተቃርኖ ሆኗል። ከአህጉሪቱ የመድረክ ተወካዮች አንድም ብሄራዊ ቡድን ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ አልቻለም።በታሪክም እጅግ በደካማና አሳፋሪ አቋም ና ውጤት ወደመጡበት ተመልሰዋል።ከዚህ ቀደም ማለትም ከ1986 የሜክሲኮ የዓለም ዋንጫ ወዲህ አህጉሪቱን ከወከሉ ብሄራዊ ቡድኖች ቢያንስ አንድ ቡድን ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ችሏል።ይህ ውጤታቸው ደግሞ እ.ኤ.አ 1998 የፈረንሳዩ የዓለም ዋንጫ የተሳታፊ አገራት ቁጥር ወደ 32 ፤የአፍሪካ ተወካዮች ደግሞ አምስት ሳይሆን ሦስት አገራት ብቻ ሆነውም ያልተቋረጠ ነበር።ከዚህ በተቃርኖ አፍሪካውያኑ በየሩሲያው መድረክ ያሳዩት የወረደ እግር ኳሳዊ ብቃት ከስፔኑ የዓለም ዋንጫ ማለትም ከሰላሳ ስድስት ዓመታት በኋላ ታይቶ የማይታወቅ አድርጎታል። በሩሲያ ምድር ከአሥራ አምስት ጨዋታ አፍሪካውያኑ ውጤት ማምጣት የቻሉት በሦስቱ ብቻ ነው።በአሥሩ ጨዋታዎች ተሸንፈዋል። ግብፅ፤ሞሮኮ፤ ቱኒዚያና ናይጄሪያ የተሰናበቱትም ገና ከምድባቸው ነበር። በተለይ በመድረኩ የተሻሉ ኮከቦችን የያዙት አገራት አንድም የረባ ጨዋታና ውጤት ሳይዙ መመለሳቸው ብዙዎችን አነጋግሯል።የኪፕቾጌ አዲስ ታሪክ\nአፍሪካ በዓመቱ ከእግር ኳስም በላይ በአትሌቲክሱ ስሟን ከፍ አድርጋ ታይታበታለች። በተለይ የኬንያው አትሌት ኢሊዩድ ኪፕቾጊ ስም ከሁሉ ገኖ ተሰምቷል። አትሌቱም በዓመቱ በማራቶን የውድድር የምንጊዜም ፈጣን ሰዓት አስመዝግቧል። አትሌቱ በጀርመን በርሊን በተካሄደው የማራቶን ውድድር 2፡1፡39 ሰከንድ በመግባት የዓለም ክብረ ወሰን ሰብሯል።የ 33 ዓመቱ አትሌት በአውሮፓውያኑ 2014 በአገሩ ልጅ ደኒስ ኪሜቶ ተይዞ የነበረውን ሰዓት በ1፡20 ሰከንድ አሻሽሎ በአስደናቂ የአሯሯጥ ብቃት የርቀቱን ክብረ ወሰን በባለቤትነት ተቆጣጥሯል። ከወራት ቀድሞም በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ማህበር የዓመቱ ምርጥ ወንድ አትሌት አሸናፊ በመሆን ልፋቱን የሚመሰክር ክብርን ተቀናጅቷል።\nየሞሃመድ ሳላህ ከፍታ\nዓመቱ አፍሪካ በድንቅ እግር ኳሳዊ ጥበብ የተካኑ ተጫዋቾች እንዳሏት ግብፃዊው የሊቨርፑሎች ኮከብ መሃመድ ሳላህ ለዓለም ያስተዋወቀበትም ነበር ።በእግር ኳሳዊ የጥበብ ልህቀቱ ዓለምን ያስደመመው ሞሃመድ ሳላህ፤ከሮማ በ 34 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ሊቨርፑል ከተዘዋወረ በኋላ በውድድር ዓመቱ በ 37 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች 31 ግብ ማስቆጠር ችሏል፡፡ሉዊስ ሱዋሬዝ 2013/14፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ 2007/08 እንዲሁም አለን ሺረር 1979 እስከ 1996 በአንድ ውድድር ዓመት ካስቆጠሯቸው 38 ጎሎች ጋር እኩል በማስቆጠር ክብረወሰኑን ተጋርቷል።በአስደማሚ ብቃቱ የሚማረኩ ወዳጆቹ ግብፃዊው ሜሲ ሲሉ የሚያሞካሹት ሳላህ፤ በተወዳጁ ሊግ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋችም ተብሎም ተመርጧል።በፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ተጫዋቾችና ጸሐፊዎች ማህበር የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች በመባል ሽልማት አግኝቷል። በዓመቱ በሁሉም ጨዋታዎች 44 ግቦችን ለሊቨርፑል ማስቆጠር ችሏል፡፡ፈርኦኖቹን ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ሩሲያው ዓለም ዋንጫ እንዲያልፉ በማድረግ የቁርጥ ቀን ልጃቸው መሆኑን አስመስክሯል። በውድድር ዓመቱ ካስቆጠራቸው ግቦች በላይም ይህች ግብ ክብርና ሞገስን አጎናፅፋዋለች።ምትሃተኛው ግራ እግር ተጫዋች በውድድር ዓመቱ ባሳያው ምርጥ ብቃት በአህጉር ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ልቆ ታይቷል።የፊፋ የአውሮፓ ዓመቱ ምርጥ ተጫዋቾች እጮዎች ውስጥም ስሙን አካቷል። ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የቢቢሲ የዓመቱ የአፍሪካ ኮከብ እግር ኳስ ተጫዋች በመሆን ተመርጧል። በዚህ ታሪኩም ከናይጄሪያዊው ኮከብ ከአውስቲን ጄይ ጄይ ኦኮቻ ጋር ተስተካክሏል። ሳላህ በውድድር ዓመቱ ባሳየው ድንቅ ብቃት የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋችነት ክብርም ተሰጥቶታል። ዓመቱም የተጫዋቹን ብቃት በማስመስከር ስሙን ከፍ አድርጎ ያስጠራባት ሆኗል።የፊፋና የአፍሪካ አገራት ፍጥጫ\nዓመቱ በተለይ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ፊፋ ከአፍሪካ አገራት ጋር እስጣ ገባውን አጧጡፎ የታየበት ሆኖም አልፏል። በተለይ ጋና፤ ናይጄሪያ ሴራሊዮን የመሳሰሉ አገራት የፊፋን ህግ በተላለፈ ሁኔታ ፖለቲካና እግር ኳስን ቀላቅለው መታየታቸውን ተከትሎ የተቋሙን ቁጣና ቅጣት አስተናግደዋል።ጋና እና ናይጄሪያ ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳደር ጋር ለገቡበት እስጣ ገባ በቶሎ ለመቋጨት በአገራቱ እግር ኳስ ውስጥ የተንሰራፋውን የአመራር ሽኩቻና ገሃድ የወጣ የሙስና ቅሌት ለማስወገድ መፍትሄ የሚሉትን እልባት ሰጥተዋል።ሴራሊዮን በአንፃሩ እንደ ናይጀሪያና ጋና የቤት ሥራዋን በሚገባ መወጣት ባለመቻሏ የፊፋን እገዳ ማስተናግድ ግድ ብሏታል።የአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ የሚስተዋለው ሙስና ከጊዜ ወደ ጊዜ ጥርሱን ማግጠጡ የታየውም በዚሁ ዓመት ነው።ተግባሩም የአህጉሪቱን እግር ኳስ በበላይነት ከሚመራው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አመራሮች ጨምሮ እስከ ብሄራዊ ፌዴሬሽን አመራሮች፤ አሰልጣኞች ዳኞችና ተጫዋቾች ዘለቆ ታይቷል።አዲሱ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ካፍ ፕሬዚዳንት አህመድ አህመድ ወደ ስልጣን እንደመጡ ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ የበላይ አካል ፊፋም ጋር በመሆን የፀረ ሙስና ፍልሚያቸውን ጀምረዋል።የጋና እግር ኳስ ማህበር ፕሬዚዳንት ክዌሲ ንያንታኪ «ስልጣናቸውን በመጠቀም ያልተገባ ጥቅም ማግኘትና ሰዎችን በማታለል 65 ሺህ ዶላር ተቀብለዋል» የሚል ክስ በመክፈት ባደረገው ምርመራ በተለይ ቁጥር «12» በሚል ርዕስ በምርመራ ጋዜጠኛው አነስ አርሜይው አናስ የተሰራው በጋና እግር ኳስ ውስጥ ስላለው ሙስና የሚያሳይ ዘገባ ፕሬዚዳንቱ ጥፋተኛ ስለመሆናቸው አረጋግጧል።በመቅረፀ ምስል የተደገፈውን ማስረጃውን የተመለከተው የፊፋ የሥነ ምግባር ኮሚቴ ግለሰቡ በብሄራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከማንኛውም የእግር ኳስ እንቅስቃሴ ዕድሜ ልክ አግዷቸዋል። ከዚህ ቅጣት ባሻገር እ.ኤ.አ ከ 2017 ጀምሮ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ካፍ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትና የእንግሊዘኛ ቋንቋ ተናጋሪ የሆኑ የአፍሪካ አገሮችን በመወከል እ.ኤ.አ ከ2016 ጀምሮ የፊፋ ምክር ቤት አባል ሆነው የሰሩትን ግለሰብ አምስት መቶ ሺ ዶላር እንዲከፍሉ ውስኗል።የአፍሪካ እግር ኳስ ምልክቶች ስንብት\nዓመቱ የአፍሪካ እግር ኳስ ምልክቶች የነበሩ ተጫዋቾች ጫማ የሰቀሉበት ሆኖም አልፏል። የቼልሲውና የአይቮሪኮስት ምልክት ዲዲየር ድሮግባ ሁለት አሥርት ዓመታት የዘለቀውን የእግር ኳስ ህይወቱን በመቋጨት ጫማ የሰቀለው በዚህ ዓመት ነው።በ24 ሚሊዮን ፓውንድ ቸልሲን በ2004 የተቀላቀለው ድርጎባ ላለፉት 8 ዓመታት በስታንፎርድ ብሪጅ የተለያዩ ድሎችን አጣጥሟል።በሰማያዊው መለያ ለ381 ጊዜያት ተሰልፎ በመጫወት 164 ግቦችን ከመረብ በማዋሃድም ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ነው። ያስቆጠራቸው የግብ ብዛትም በቼልሲ አራተኛው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ያደርገዋል። ስታምፎርድ ብሪጅን እንደቤቱ የሚመለከተው ድሮግባ፤ አወዛጋቢው የሚል ቅጽል ያላቸው ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ «በአውሮፓ ምርጡ ተጫዋችና መልካም ስብዕና ያለው» ሲሉም ያንቆለጳጵሱታል።በሰማያዊዎቹ ቤት ቆይታውም፤አራት የፕሪምየር ሊግና የኤፍ ኤ ዋንጫዎችን አንስቷል።ሦስት የሊግ ካፕ፣ ሁለት ኮሚዩኒቲ ሺልድ እንዲሁም በ2012 የውድድር ዓመት አንድ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫም አሳክቷል።ኢኳቶሪያል ጊኒ እ.ኤ.አ 2015 ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ ጋናን በመርታት ዋንጫውን ለማንሳት ችሏል።የፈርኦኖቹ ግብ ጠባቂ አል ሃድሪ ከሩሲያው የዓለም ዋንጫ ማግስት በ45 ዓመቱ ራሱን ከእግር ኳስ ያገለለበት ዓመትም ነው። በ 22 ዓመታት ቆይታው በክለብም ሆነ በብሄራዊ ቡድን በድል የተንቆጠቆጡ ዓመታትን አሳልፏል።የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅ እጦት\nካፍ በቀጣዩ ዓመት የሚካሄደው የአፍሪካ ታላቁ የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለማዘጋጀት የተቸገረበት ዓመት ነበር። አሁን ባለው ሁኔታ ለ2019 የአፍሪካ ዋንጫ 13 አገራት ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።ይሁንና ከዝግጅት ማነስ ጋር በተያያዘ የአፍሪካ እግር ኳስ በበላይነት የሚመራው ተቋም መድረኩን የሚያዘጋጅለት አገር በማጣት ሲባክን ቆይቷል።ከዝግጅቱ ሂደት መዘግየት ጋር ተያይዞ ካፍ ለካሜሮን ተሰጥቶ የነበረውን የዘንድሮው የአፍሪካ ታላቅ የእግር ኳስ ሁነት የአዘጋጅነት ሚናን ነጥቋል።ይህንን ተከትሎም በአጭር ጊዜ ውስጥ ውድድሩን የማስተናገድ አቅምና ፍላጎት ያላቸው አገራት በማማተር ሲባክን ታይቷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2011ታምራት ተስፋዬ", "passage_id": "6ac1b2bd4b1f51a892636ab382aac5be" }, { "passage": "አንድ ገበሬ ናቸው። በዘመናቸው ሮጠው ያሻቸውን አድረገዋል፤ አንሰተው ጥለው እንዳላለፉ ሁሉ ዕድሜ ገሰገሰና ጉልበታቸው ከዳቸው። ጊዜ ሲገፋ አቅማቸው ሲደክም እጅ ሰጡ። በወጣትነታቸው ሌላውን የጦሩት ያህል ተረኛ መሆን ግድ አላቸው። ግን ደግሞ እድለኛ አልነበሩምና ‹‹ጧሪዬ ይሆናል›› ብለው ተስፋ የጣሉበት አንድያ ልጃቸው እስር ቤት ይገባል። ለዚያው ለገበሬ ወሳኝ በሆነው የአዝመራ ወቅት። ይህ ወቅት ገበሬው አቅሙን አሟጦ የሚጠቀምበት ነውና ሽማግሌው መሬታቸው ጦሙ ማደሩን ሲረዱ ሀሳብ ገባቸው። እናም ለልጃቸው\n‹‹ልጄ አቅሜ እንደደከመ ጉልበቴ እንደዛለ ታውቃለህ። ዘንድሮ አንተም የለህ መሬቱ ፆሙን ማደሩ ነው። የአንተ መታሰርና ከእኔ መለየትን\nሳስብ መጪው ጊዜ አስጨንቆኛል። በርሃብ መሞቴ ነው። መሬቱን ማን ቆፍሮና አለስልሶ አዝመራውን ይዘራልኛል? ችግር ውስጥ ወድቄብሃለሁ።››\nበማለት ወደ እስር ቤት ደብዳቤ ላኩ። ልጃቸው የአባቱን\nመልዕክት አንብቦ ምላሽ ፃፈ። ‹‹አባቴ ዘንድሮ ሌላ ሰው የሚያግዝህ ቢኖር እንኳን የአዝመራውን ቦታ እንዳታስቆፍረው። አይዞህ!\nአምላክ ሌላ መፍትሄ ያቀርብልናል። የገደልኳቸውን ሰዎች የቀበርኩት እዚያ ቦታ ላይ ስለሆነ በፍፁም እንዳይቆፈር ሌላ ሰው ከቆፈረው\nማስረጃ ይገኝብኛል፤ አደራ›› ብሎ መልዕክቱን ይመልሳል። ይህ መልዕክት ከተላከ\nከጥቂት ቀናት በኋላ አባት ለልጃቸው በድጋሚ ደብዳቤ ላኩ። ‹‹ልጄ በጣም አመሰግንሃለሁ፤ ባለፈው የላከው ደብዳቤ እኔ ዘንድ ከመድረሱ\nበፊት ፖሊሶች አይተው ነበርና ማሳውን ሲቆፍሩ ከረሙ። ምንም አይነት ሬሳ ግን አላገኙም፤ ይህንን ያደረከው ቁፋሮው በዘዴ በእነሱ\nእንዲፈፀም አስበህ መሆኑን ተረድቻለሁ። እናም እነሱ በቆፈሩት ማሳ ላይ አዝመራዬን ዘርቼ እፎይ ብያለሁ። ልጄ እዚያም ሆነህ እገዛህ\nስላልተለየኝ እጅጉን አመሰግናለሁ›› አሉት።እናም ምን ለማለት ነው ወዳጆቼ፤ የቀረበንን\nመጥፎ አጋጣሚ በመላ ብናልፈው አጋጣሚውን በመልካም ብንጠቀመው መልካም ነው። ‹‹የተወረወረብህን ጠጠር ለቅመህ መልሰህ ከመወርወር\nይልቅ መሸጋገሪያ ድልድይ ስራበት›› የሚል ምክር ተደጋግሞ ይደመጣል። ልክ ነው። ስለማን ብለን መጥፎ አጋጣሚዎችን መጥፎነታቸው\nላይ ብቻ በማተኮር እንቆዝማለን? ይልቅ መጥፎ ገጠመኙን እራሱን መግጠም የተሻለ ነው። በየዕለት እንቅስቃሴያችን የገጠመን አስቸጋሪ\nጉዳይ ወደ ጥሩ አጋጣሚና ጥቅም የመለወጥ ልማዳችን ምን ያህል ይሆን? ያሰብነው አልሰምር፤ ያቀድነው አልሳካ ቢለን ፈፅሞ ወደ ተስፋ\nመቁረጥ መገባት የለበትም። ስንት ነገር ከፊታችን እያለ በአንድ ሙከራ መሳካት አለመሳካት እጅ ከተሰጠማ መነሻችን ላይ ለጉዳዩ የሰጠነው\nቦታ ትልቅ መሆኑ እንጂ ገና ስናስበው ላይሳካ እንደሚችል አላስተዋልንም ማለት ነው። በነገራች ላይ ሙከራ የሚሳካው አልፎ አልፎ\nእንጂ ሁሌም አይደለም፤ የስኬታማ ሰዎች ገጠመኝና የህይወት ውጣ ውረድ ብንመረምር መንገዱ አልጋ ባልጋ ሆኖለት ያለፈ አይገጥማችሁም።\nበጉዛችን ውስጥ ወደኛ የሚቀርቡን መጥፎ አጋጣሚዎች ወደ መልካም ገጠመኝ መለወጥ እርግጥ የሚያወሩትን ያህል ቀላል አይደለም። ነገር\nግን አንዴ ያ መጥፎ አጋጣሚ ወደኛ መጥቷልና ፈጥሮብን የሚያልፈው ጉዳት ከመቀበል ይልቅ ወደ በጎ አጋጣሚ መለወጡ ግድ ይለናል።\nብዙ ጊዜ የበጎ ነገሮች አልያም የግኝቶች መነሻ\nአስቸጋሪ ወይም መጥቶ አጋጣሚዎች ናቸው። እንደውም በችግር ምክንያት የተፈጠሩ መፍትሄዎች የሰው ልጅ ኑሮ ሲያቀሉ በተደጋጋሚ አስተውለናል።\nዛሬ ላይ አለም ጭለማን የረታበት ብርሃን ወይም መብራትን የፈጠረው ቶማስ ኤድሰን እጅጉን ጭለማ ይፈራ እንደነበር እናውቅ ይሆን?\nጭለማን መፍራት ደግሞ ጭለማን ለመግፈፍ እንዲማስን አደረገውና መፍትሄ ወለደለት።እናም መከራ መፍትሄን ይወልዳል፤ ፍርሃት ማምለጫን\nያበጃል። ድህነትን አጥብቆ የሚፈራ ሰው ከድህነት ለመውጣት ብርቱ ጥረት ያደርጋል። እራሱን ለመለወጥ ለሊት እና ቀን ሲማስን እራሱን\nየተሻለ ቦታ ላይ ለማድረስ ሁሌም ሲፍጨረጨር የተሻለ ቦታ ላይ መገኘቱ አይቀሬ ነው። እየንዳንዱ መጥፎ ገጠመኞቻችንን ወደ እድል\nእና መልካም አጋጣሚ መቀየር መቻላችን ጥቅሙ ያየለ የሚያደርገው ለዚሁ ነው። ውዶቼ አንድ ነገር ካስተዋልን ብዙ ጊዜ የኛ\nስኬት መቃረቢያ የሚሆኑ ጉዳዮች ትኩረት የሰጠንባቸውና እንዳይደናቀፉብን ጠንቃቃ የሆንባቸው ጉዳዮች ናቸው። ስለ ጉዳይ አስልተን\nመመርምር ጉዳዩን ጠንቅቀን ማወቅና በዚያ ዙሪያ ያለንን ሁኔታ ምቹ ማድረግ እንዳለብን ፍላጎታችን ያስገድደናል። የጀመርነውን ጉዳይ\nከዳር ለማድረስ መውተርተራችን ፍሬ ያፈራል። ነገር ግን ስኬትን አልመን የጀመርነው ጉዳይ ዋነኛ እና ወሳኝ ነው። ያመንበትን ሳይሳካልን\nቢቀር አለመሳካቱን መነሻ አድርገን ያልተሳካበት ምክንያት መመርመር ተገቢ መሆኑ አያጠያይቅም። ያ ጉዳይ የኛ የመጨረሻ አማራጭ አድርገን መውሰዳችን\nየመጀመሪያው ስህተት ነው። አለም በብዙ ገጠመኞች የተሞላች ለሰው ልጆች ሰፊ ዕድልን ይዛ የቀረበች ሆና ሳለ የኛ ምልከታ ውስን\nይሆንና አንድ መንገድ ላይ ብቻ ችክ እንላለን። ያ መንገድ ደግሞ የሚጓዙበት ብዙዎች ናቸውና የተጣበበ ሆኖ ይጠብቀናል። አስፍቶ\nመመልከትና ሌሎች አማራጮችን ማየቱ የኛ ልምድ ሊሆን ይገባል። በጥረታችን ውስጥ የሚገጥመንን ጋሬጣ መመንጠር የሚያስችል አቅም ይዞ\nመገኘትና መፋለም፤ ይህን የማድረግ አቅምን ከፈጠርን ሌላ ዘዴ መዘየድና ችግሩን እራሱ በመፍትሄነት መጠቀሙ ልምድ ብናደርግ መንገዶች\nሁሉ ይቀናሉ። አዲስ ዘመን ታህሳስ 20/2012ተገኝ ብሩ ", "passage_id": "9526bdf2d33bb41a59c50780d0b1f80b" }, { "passage": "‹‹ኢትዮጵያውያን ለዓድዋ ድል ማንንም ዕርዳን እንዳላሉት ሁሉ አሁንም ለሰው ልጆች በበራው ችቦ በዓባይ ላይም ሊደግሙት ይገባል፡፡›› የታሪክ ተመራማሪምሥጋና ለ1881ዓ.ም አንቀፅ 17 ስምምነት ይሁንና የጣልያን መሠሪነት ስህተት በፈጠረችው አለመግባባት የጥቁሮችን ሥነ ልቦና ከአምሳለ ዝንጀሮነት፣ ከኋላቀርነት መንጋጋ ፈልቅቆ በአሸናፊነቱ ማማ የሚያስቀምጥ ገድል እንዲፈጠር መሠረት ሆኗል፡፡ ከንቱ የቅኝ ግዛት ሐሳቦቻቸው የጥቁሮችን እኩልነት በስልትም በጦርነትም በልጦ የማሳየት ሞራል አልነበራቸውም፡፡ የጣር ትግሎቻቸውን በቴክኖሎጂዎቻቸው አምነው፣ ለቀለም አብዮቶቻቸው የተፋለሙት ጣልያኖች ‹ያሉት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ› ብለው በሚያምኑት ልበ ሙሉ ኢትጵያውያን እጅ ከመስጠት አልዳኑም፡፡ የወራሪዎን የትዕቢት ተራራ አፈራርሶ፣ የቅኝ ገዥ የበላይነት ፍኛን አስተንፍሷል፤ በሀገር ውስጥ የነበሩ አንጃ እሳቤዎችን ነቅሎ የአንድነት ምሰሶዎችን አጥብቋል፤ ዓድዋ፡፡ አሜኬላዎች ደቅቀው ለአፍሪካ ወንድሞቻቸው የቅኝ ተገዥነትን የጀርባ እሾህ መንቅረው እንዲያወጡ የንጋት ብርሃን ሆኗል፤ ዓድዋ፡፡ኢትዮጵያውያን የዓድዋ ድልን ለማግኘት ከውጪ ጠላት ብቻ ሳይሆን ከውስጣቸው የጭቃ እሾህ ጋርም ተፋልመዋል፤ ስህተቱን ያረመውን በይቅርታ፣ አልመለስ ያለውን በኃይል ከልክ አስገብተው ነው ወደ ድል የደረሱት፡፡ ‹‹ኧረ ጠላትማ ምንጊዜም ጠላት ነው፣አስቀድሞ መግደል አሾክሿኪውን ነው›› ብለው ከውጭ ወራራ ኃይል የተቃጣውን ኢትዮጵያዊነትን የማፍረስ ዓላማ እውን እንዳይሆን በኋላ ቀር መሣሪያና ዘመናትን በሚሻገር ወኔ ተዋግተዋል፡፡ ይህን እውነት ፈረንሳዊው የታሪክ ተመራማሪ ፋብሪስ ዲ አልሚዳ (Fabrice d’Almeida) ‹‹እኛ የሰለጠንን ነን የምንል ሕዝቦች ኋላቀር ናቸው ከምንላቸው ኢትጵያውያን ብዙ የምንማረው ነገር አለን፤ ኢትዮጵያውያን ለአንድ ጥይት ይሳሳሉ፤ የሚገድል ካልሆነ በቀር አይተኩሱም፤ ለዚያውም ቢሆን በ10 እና በ15 ያርድ ቀርበው በአንድ ጥይት ሁለት ሰው ደራርበው መግደል ይፈልጋሉ፤ ይህ ካልሆነ ተደበላልቀው በጎራዴ መምታት ይመርጣሉ እንጂ ጥይት ማበላሸት አይፈልጉም›› ብሏል፡፡የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህር እና ተመራማሪው አየነው መሠለ (ዶክተር) ‹‹የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውያን አንድነት ኃይል የማይሰብረው ማንኛውም የውጭ ኃይል እንደሌለ ማሳያ ነው›› ይላሉ፡፡ ያነከሰ የፍትሕ ሚዛን ማብቂያ፣ የፖለቲካና የታሪክ ርሃቦች አብቅተው የሁሉም የሰው ልጆች ታሪክ መጀመሪያ የተበሰመሆኑን ተናግረዋል፡፡ ‹‹የጣልያን ውርደትና የኢትዮጵያውያን ድል ለመላው ዓለም የተደበላለቀ ስሜትን የፈጠረ ነበር›› ያሉት ዶክተር አየነው በመላው አፍሪካ የተለያዩ ሀገራት የኢትዮጵያን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ የነፃነት ምልክት አድርገው ለነፃነት ትግል በሚያመቻቸው መልኩ እንደወሰዱም ገልጸዋል፡፡‹‹ኢትዮጵያኒዝም›› የሚባል የፖለቲካ እሳቤ እና የማሸነፍ ወኔዎች፣ ‹‹ለባርነት እምቢ አልገዛም›› የሚሉ ድምፅች ከመቼውም ጊዜ በላይ ጎልተው የወጡበት የዓድዋ ማግሥት መሆኑን ምሁሩ አስረድተዋል፡፡ ‹‹ምናልባትም ይህን ጦርነት ኢትዮጵያ ባታሸንፍ የዓለም ታሪክ የነጮችን የበላይነትና የጥቁሮችን ባርነት መሠረት እንደያዘ ይቀጥል ነበር፡፡ ጥቁር ሕዝቦችም ገበያ ላይ ከሚሸጡ ዕቃዎች በተለየ መንገድ ለመታየት ዕድል አያገኙም ነበር፡፡ ስለዚህ የተከፈለልን ደም በምክንያት ነው›› ብለዋል ዶክተር አየነው፡፡የዓድዋ ድል ግራ ያጋባቸው ጣልያኖች በሚላን፣ ቱሪንና ኔፕል ከተሞች የተለያዩ የተቃውሞ ጭኸቶችን በራሳቸው መሪዎች ላይ አሰምተዋል፡፡ መጋቢት 9 ቀን የጣልያን የወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በሕዝቡ ቁጣ ምክንያት ወረዱ፡፡ ሰልፈኞቹ ከራሳቸው ንጉሥ ይልቅ የጥቁሮቹ ንጉሥ ግርማ አላስተኛቸውም ‹‹ፍራንሲስኮ ይውረድ፤ ዳግማዊ አጼ ምኒልክ ይንገሥ›› በሚሉ ድምፆች የራደው መንግሥት ሐሳቡን እርግፍ አድርጎ ትቶ ተደብቋል፡፡የጦር መሪዎች በሀፍረት መግቢያቸውን አጥተው ገሚሱ ወህኒ ወረዱ፤ ገሚሱ ቀና ብሎ ማየት የማይችል ሆኖ ቅስሙ ተሰብሮ ኖረ፡፡ ‹‹አውሮፓውያን በጣልያናውያን ይሳለቁ ስለነበር ጣልያን እንቅልፍ አጥታ ነበር›› ያሉት ዶክተር አየነው ሌሎች ቅኝ ገዥ ሀገራት በኢትዮጵያውያ ድል በመራድ ጦራቸውን ማደራጀት እና ቅኝ ተገዥዎችን በጥቅም የመደለሉ ሥራ ጎልቶ የወጣበት ወቅት እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡በደቡብ አፍሪካ፣ አሜሪካ እና ፈረንሳይ ልዩ የድል ችቦዎች እና ደስታ ፈንጠዝያዎችን አስከትሏል፤ የዓድዋ ድል፡፡  ለቅኝ ገዥዎች ሰደድ እሳት ሁኖ አንገታቸውን ደፍተው ሲሄዱ ለኢትዮጵያውያን ደግሞ ከድል ማግሥትም የተፈጠረው የአንድነት ስሜት ልዩ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ዳግማዊ አጼ ምኒልክ ከድል በኋላ በርካታ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቶች ከአውሮፓና አሜሪካ ሀገራት ደርሷቸዋል፤ ፎቶዎቻቸውን ማየት የሚፈልጉ ሀገራትም መልስ እንዲላክላቸው የሚሹ እንደነበሩ ምሁሩ አስታውሰዋል፡፡ የወዳጅነት በሮችም በኢትዮጵያ ተከፍተው የቅኝ ገዥዎችን ዘመን ፍጻሜ ለማቅረብ ኢትዮጵያ የጦርነት ስልት ማሰልጠኛ፣ የወኔ ስንቅ በመሆን ለመላው አፍሪካውያን ማገልገሏን ቀጠለች፡፡የጥቁርን ማንነት ከባርነት የተፈጥሮ ሕግ ጋር ያስተሳሰሩ በአሜሪካ የሚኖሩ ጥቁሮች መጻፍና መማር እንዳይችሉ ይደረጉ ነበር፡፡ ይህንን ሲያደርግ የተገኘ ደግሞ እጁ ይቆረጥና ዓይኑ ይወጣ ነበር፤ ዓድዋ ግን ከእነዚህ ሰዎች እጅ አትርፏል፤ የእነዚህን ሰዎች ዓይን ብቻ ሳይሆን ሰውነታቸውን መልሶላቸዋል፡፡‹‹ይህ በጥቁሮች እና በነጮች መካከል የተደረገ ተራ ጦርነት ብቻ አይደለም›› ያሉት የሀርቫርድ ዩነቨርሲቲው የታሪክ መምህርና ተመራማሪ ራይሞንድ ጆንስ (ፕሮፌሰር) ‹‹በነጮች ውስጥ የነበረውን ‹ጥቁሮች አይችሉም፤ ባሮች ናቸው› የሚለውን የሰበረ ነው፤ በጥቁሮች ውስጥ የነበረውን ጎደሎነት ሰርዞ ከነጮች በላይ የመሆን ችሎታ እንዳላቸው ያረጋገጡበት የሰውነት ልክ ነው›› ብለዋል፡፡ የበርሊኑ የአፍሪካን የዳቦ ክፍፍል ማርከሻ መድኃኒቱ ዓድዋ መሆኑን አልገመቱትም፡፡", "passage_id": "de01a9646bc2de24d918db5db7e4b7d2" }, { "passage": "ብዙ ወይም የበለጠ የመሻት ስሜት አንዳንድ ጊዜ በአስተዳደጋችን ወይም በባህላችን የተነሳ ከውስጣችን የሚጠፋበት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡ ስለዚህም ከህይወት የምንጠብቀው ዝቅ ያለና ከዕፁብ ድንቅ ያነሰ ነገር ይሆናል፡፡ ሆኖም ተስፋ ልንቆርጥ አይገባም፡፡ ለስኬት ያለን ፍላጐት ዳግም ሊነቃቃና ሊነሳሳ ይችላል፡፡ ዳግም ዕፁብ ድንቅ ህይወት ልንሻ እንችላለን፡፡ ከስኬት ጋርም ቤተኛ እንሆናለን፡፡ ስኬት ሁሉ ግን ስኬት እንዳልሆነ ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ አንዳንዶች ህይወታቸውን ሁሉ የስኬትን መሰላል ሲወጣጡ ከርመው የማታ ማታ መሰላሉ ትክክለኛው ግድግዳ ላይ ተደግፎ እንዳልነበረ ይገነዘቡታል - እናም ስኬታቸው ትክክለኛው ወይም እነሱ የሚሹት አልነበረም ማለት ነው፡፡ ለዚህም ነው ትክክለኛውን ስኬት መቀዳጀታችንን ማረጋገጥ ያለብን፡፡ የእኛን የተሟላ ሰብዕናና ችሎታ በአስደናቂ መንገድ መግለጽ የሚችል ሊሆን ይገባል ስኬታችን፡፡ ስኬት አንዲት ነጠላ ሁነት ወይም ውጤት አይደለችም - በውስጣችን ያለ ድንቅ ተሰጥኦ መገለጫ እንጂ፡፡ ዓለም ይሄንን ተሰጥኦ የበለጠ ሰዋዊና የበለጠ ውብ እንድናደርገው ህልቆ መሳፍርት ዕድሎችን ታቀርብልናለች፡፡ ተሰጥኦአችንን ወይም የነፍሳችንን ጥሪ ፈልጐ ማግኘት ግን የኛ ተግባር ነው፡፡ እውነተኛ ስኬት ለማሸነፍ ሲባል ብቻ የማሸነፍ ጉዳይ አይደለም፡፡ ቲሞቲ ጋልዌይ የተባለ የስኬት ሊቅ እንዲህ Y§L- ..ማሸነፍ አንድ የሆነ ግብ ላይ ለመድረስ መሰናክሎችን ማለፍ ነው፤ የአሸናፊነቱ ትልቅነት የሚለካው ግን በተደረሰበት ግብ ትልቅነት ነው..ሆኖም ግን የማሸነፍ አባዜ ተጠናውቶን ብቻ የምንቀዳጀውን ጊዜያዊ ስኬት ህይወታችንንና የሌሎችን ህይወት ከሚያበለጽግልን ዘላቂ ስኬት መለየት መቻል አለብን፡፡ ትክክለኛውና ዘላቂው ስኬት የዓለምን ሃብት በከፍተኛ ሁኔታና ያለብዙ ብክነት ጥቅም ላይ ያውላል፡፡ የስኬት መርሆች ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል ተስፈኝነት (ደግ አሳቢነት) አንዱ ነው፡፡ ትላልቅ ችግርና መከራዎችን አሸንፈው ስኬትን የተቀዳጁ ሰዎች ሁሉ ምስጢር እንደሆነም ይነገራል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ፣ ኧርነስት ሻክሌተን፣ ኢሊኖር ሩስቬልት - የመከራ ጊዜያቶችን ተቋቁመው ለማለፍ ያስቻላቸው በአዎንታዊ ነገሮች ላይ የማተኮር ችሎታቸው እንደሆነ በይፋ ይቀበላሉ፡፡ እኒህ ሰዎች ክላውዴ ብሪስቶል የተባለው ሊቅ ..የእምነት ተዓምራዊ ሃይል.. የሚለው ነገር ገብቶአቸዋል ማለት ነው፡፡ ታላላቅ መሪዎች እንዲሁ ደረቅ እውነታን ፊት ለፊት የመጋፈጥ ያልተለመደ ችሎታ እንዳላቸው ይነገራል፡፡ ለዚህ ብቸኛ ሃይላቸው አድርገው የሚቆጥሩት ደግሞ ቆራጥነት የተመላበትን ተስፈኝነታቸውን ነው፡፡ ተስፈኛ ሰዎች የሚሳካላቸው ነገሮች ጥሩ ይሆናሉ ብለው ስለሚያምኑ ብቻ አይደለም፤ ስኬትን መጠበቃቸውም ተግተው እንዲሰሩ ስለሚያደርጋቸው ጭምር ነው፡፡ ከህይወት የምንጠብቀው ትንሽ ነገር ከሆነ ትንሽ ሙከራ እንኳን ለማድረግም አንነሳሳም፡፡ ከፍ ያለ ነገር ስንጠብቅ ብቻ ነው ጥረታችንም ከፍ ያለ የሚሆነው፡፡ ስኬት የታመቀ ጥረት ይፈልጋል፡፡ አብዛኞቹ ሰዎች ጉልበታቸውን (ሃይላቸውን) በብዙ ነገሮች ላይ ይበታተኑታል፡፡ በዚህም የተነሳ በምንም ነገር የላቀ ውጤት ማስመዝገብ ይሳናቸዋል፡፡ ኦሪስን ስዌት ማርደን ይሄን በተመለከተ ሲናገር ..ዓለም ጠበቃ፣ ሚኒስትር፣ ሃኪም፣ ገበሬ፣ ሳይንቲስት ወይም ነጋዴ እንድትሆን አትጠይቅህም፤ መስራት ያለብህን አትነግርህም፤ ነገር ግን በምትሰራው ማናቸውም ሥራዎች የበቃህ እንድትሆን ትጠይቅሃለች..ስለዚህም ስኬታማ ለመሆን የላቀ ዓላማና ግብ ሊኖርህ ይገባል፤ ያንን ለማሳካትም በቁርጠኝነት ጥረትህን መግፋት አለብህ፡፡ የዓለም ሥልጣኔ ጐህ ሲቀድ አንስቶ የነበሩ ታላላቅ መሪዎች ሁሉ የየራሳቸው ህልም የነበራቸው ናቸው፡፡ ህልም ሳይኖርህ ስኬት የሚታለም አይደለም፡፡ ሃብትና ብልጽግናን በምናብህ ሳትቀርጽ በባንክ ሂሳብህ ውስጥ ከቶውንም ልታይ አትችልም፡፡ የሚቀድመው የምትሻውን በምናብህ መሳል ነው፡፡ ከዚያም በእውንህ ታየዋለህ፡፡ ግን ህልም ከየት ይፈጠራል? Think and Grow Rich  (አስብና በልጽግ እንደማለት) የተሰኘው ድንቅ መጽሐፍ ደራሲ ናፖሊዮን ሂል፤ ህልም እንደ እሳት ከሚንቀለቀል ውስጣዊ ፍላጐት ይወለዳል ይለናል፡፡ ህልም ከችላ ባይነት፣ ከስንፍና ወይም ከፍላጐተ - ቢስነት አይፈጠርም፡፡ የስኬታማ ሰዎች ሌላው መርህ ለመሥራት ፈቃደኛ መሆን ነው - አንድ ድንቅ የሆነ ነገር ለመፍጠር ሁሌም ተግተው ይሰራሉ፡፡ ተግተን በሰራን ቁጥር ስለራሳችን አንድ ነገር እናውቃለን፡፡ የስኬት ህግ እንደሚለው አንድ ጊዜ ስኬትን ከተቀዳጀን እንዲዘልቅ የሚያደርገው ሁኔታ ራሱ ይፈጥራል፡፡ እንደ ስኬት የሚቀጥል ምንም ነገር የለም ይባላል፡፡ ዘላቂ ስኬት የሚገነባው በዲሲፕሊን ላይ እንደሆነ ማወቅ ብልህነት ነው፡፡ ለራሳችን ትዕዛዝ መስጠትና ትዕዛዙን መከተል መማር አለብን፡፡ ይሄ ጉዳይ ለጊዜው አሰልቺ ሊመስለን ይችላል፡፡ የረዥም ጊዜ ውጤቱ ግን አስደማሚ ይሆናል፡፡ ታላላቅ ስኬታማ ሰዎች ዩኒቨርስ የተገነባው በአቶሞች እንደመሆኑ ስኬት ደግሞ በእያንዳንዷ ደቂቃ እንደሚገነባ አሳምረው ÃWÝlù””በእርግጥ ለዛሬው ዘመን ህልመኞች ትዕግስትና ክፍት አዕምሮ ወሳኝ ጉዳዮች ናቸው፡፡ አዳዲስ ሃሳቦችን ለመቀበል የሚፈሩና ዝግጁ ያልሆኑ ሰዎች ገና ሳይጀምሩ ያከተመላቸው ናቸው፡፡ ልትሰራ የምትፈልገው ነገር ትክክለኛና የምታምንበት ከሆነ ሳታወላውል አድርገው ይላል ናፖሊዮን ሂል፡፡ እወድቃለሁ ብለህ አትፍራ፡፡ እያንዳንዱ ውድቀት አቻውን የስኬት ዘር ይዞ ይመጣልና፡፡ የስኬትና የብልጽግና ሌላው መርህ ጥብቅ የሆነ እምነት ነው፡፡ በእርግጥ አንድን ነገር መፈለግ ወይም መመኘትና የፈለጉትን ነገር ለመቀበል ዝግጁ መሆን የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ ማንም ሰው አንድን ነገር እንደሚያገኘው እስካላመነ ድረስ ለዚያ ነገር ዝግጁ ነው ማለት አይቻልም፡፡ አዕምሮው ተስፋና ምኞት ላይ ሳይሆን እምነት ላይ ማተኮር አለበት፡፡ ያውም ጥብቅና የማይናወጽ እምነት፡፡ ያኔ ነው ያሻውን በእጁ የሚያስገባው፡፡ ለእምነት ደግሞ ክፍት አዕምሮ ወሳኝ ነው፡፡ የዝግ አዕምሮ ባለቤቶች ለማመን አይነሸጡም፤ ናፖሊዮን እንደሚለው፡፡ ምናብ ዕቅዶች የሚፈጠሩበት ዎርክሾፕ ነው ይላል - ሂል፡፡ ፍላጐትህ መልክና ቅርጽ የሚይዘው እንዲሁም ወደ ተግባር የሚለወጠው በምናብህ እገዛ ነው፡፡ በምናብህ የቀረጽከውን ማናቸውንም ነገሮች መፍጠር ወይም ማድረግ ትችላለህ፡፡ ለተግባር ቸልተኛ ከሆንክ የምናብህ አቅም እየተዳከመ ሊመጣ ይችላል፡፡ ሙሉ በሙሉ ባይሞትም ለጊዜውም ቢሆን ያንቀላፋል፡፡ ሆኖም ጥቅም ላይ ስታውለው ከእንቅልፍ ሊነቃና ሊታደስ ይችላል፡፡ ራስህን ካላሸነፍክ በራስህ ትሸነፋለህ ይላል - ናፖሊዮን ሂል በመጽሐፉ፡፡ የውድቀት ዋና ሰበቡ ለውሳኔ ዳተኛ መሆን ወይም መወሰን አለመቻል ነው፡፡ የሌሎች ሃሳብ ወይም አስተያየት ተጽእኖ የሚያሳድርብህ ዓይነት ሰው ከሆንክ የራስህ ፍላጐት አይኖርህም፡፡ የራስህን ውሳኔ በመወሰንና በመከተል ለራስህ ፍላጐት ተገዢነትህን አሳይ፡፡ የራስህ ሃሳብና አዕምሮ እንዳለህ አትዘንጋ፤ ስለዚህም ተጠቀምበት፡፡ በእርግጠኝነትና በፍጥነት ውሳኔ ላይ የሚደርሱ ሰዎች የሚፈልጉትን ያውቃሉ ብቻ ሳይሆን ያገኙታልም፡፡ በየትኛውም የህይወት ዘርፍ ላይ የሚገኙ መሪዎች በፍጥነትና ፈርጠም ብለው የሚወስኑ ናቸው፡፡ ለዚህም ነው መሪ የሆኑት፡፡ የሁሉም ስኬት መነሻ ፍላጐት ነው፡፡ ፍላጐታችን ደካማ ሲሆን ውጤቱ ደካማ ይሆናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ሃብትና ስኬት አጥብቀው ሊፈልጉ ይችላሉ፡፡ ችግሩ ግን ጽናት ይጐድላቸዋል፡፡ የሚፈልጉትን ለማግኘት በሚያልፉት ሂደት በሚገጥማቸው ትንሽ ፈተና ወይም መሰናክል እጃቸውን ይሰጣሉ፡፡ ይሸነፋሉ፡፡ ገንዘብና ሃብት ወይም ስኬት ቶሎ የሚሳቡት አዕምሮአቸው እነዚህን ለመቀበል ዝግጁ ወደሆኑት ነው፡፡ ድህነትም የሚሳበው ድህነትን ለመቀበል ዝግጁ ወደሆነው አዕምሮ ነው፡፡ የጽናትን ልማድ ያዳበሩ ሰዎች የሽንፈት ዋስትና አላቸው፡፡ የቱንም ያህል ጊዜ ቢሸነፉ በመጨረሻ የስኬት ጣራ ላይ መውጣታቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ", "passage_id": "f6d233723ff027c71b563ed4f9e876ad" } ]
4ba3d527262773d086c4d7006808dd58
970212ebffe10d472dadf92cf4845dd0
አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የእገዳ ውሳኔውን አነሳ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌቶች ተወካዩ ሚስተር ሁሴን_ማኪ ላይ አሳልፎት የነበረውን የእገዳ ውሳኔ አነሳ። በዶሃው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ላይ በማራቶን ውድድር ተሳትፈው የነበሩ አትሌቶች ከማገገሚያ ሦስት ወራት በፊት ውድድር እንዳያደርጉ ውሳኔ አሳልፎ የነበረ ቢሆንም በሚስተር ሁሴን ማኪ ወይንም ‹‹Elite Sport Management›› ስር ያሉ የተወሰኑ አትሌቶችን በኒውዮርክ ማራቶን ውድድር ላይ መሳተፋቸውን ተከትሎ ፌዴሬሽኑ ከተወካዩ ሁሴን ማኪ ጋር የነበረውን ውል እንዳቋረጠ ይታወቃል:: ፌዴሬሽኑ ከትናንት በስቲያ ከሰዓት በኋላ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ግን ይህን የውል ማቋረጥ እገዳ እንዳነሳ አሳውቋል፡፡ በመሆኑም ውሳኔውን የሰሙት ማናጀሩ የይቅርታ ደብዳቤያቸውን ለፌዴሬሽኑ ከማስገባታቸውም በተጨማሪ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግንዛቤ በማስገባታቸው ከሚኖሩበት አሜሪካ ተነስተው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ቢሮ ድረስ በአካል በመቅረብ ስህተታቸውን አምነው ይቅርታ እንዲደረግላቸው በመጠየቃቸው ፌዴሬሽኑ ጥያቄያቸውን በሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በኩል ከመረመረ በኋላ ይቅርታቸውን ተቀብሎ እርምጃው ለሌሎችም አስተማሪ ይሆን ዘንድ ወደ ገንዘብ ቀይሮላቸዋል። የፌዴሬሽኑ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በመግለጫው ወቅት ለጋዜጠኞች እንዳስረዱት ሚስተር ሁሴን ማኪ ከ120 በላይ ስመጥር አትሌቶችን ይዘው ለ13 ዓመታት ከፌዴሬሽኑ ጋር እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ በአራቱም የአገሪቱ ዋና ዋና ቦታዎች የታዳጊዎች አትሌቲክስ ፕሮጀክት ከፍተው እየሠሩ ከመሆናቸው ባሻገር፣ በአዲስ አበባ ቢሮ ከፍተው እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናና በኦሊምፒክ በርካታ ውጤታማ አትሌቶችን ለአገራችን ማፍራታቸውን ከግምት በማስገባት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ይቅርታቸውን ተቀብሎ ቅጣታቸውን ወደ ገንዘብ ሊቀይር ችሏል፡፡ እገዳው በሃያ አምስት ሺ የአሜሪካን ዶላር እንደተቀየረላቸው የተገለጸ ሲሆን ቅጣቱ በቂ ነው ባይባልም ሌሎች እንዲማሩበት ውሳኔው መተላለፉን ኮማንደር ደራርቱ አብራርታለች፡፡ አዲስ ዘመን ኅዳር10/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22840
[ { "passage": "የኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን የዘጠኙ የክልልና የ2ቱ ከተማ መስተዳድር እግርኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንቶች፣ የስፖርት ኮሚሽን አመራሮች እና የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አመራሮች በተገኙበት የውይይት መድረክ ከብዙ ውይይቶች በኋላ ነው ውሳኔው ውድቅ የሆነው።እንደ ምክንያት የቀረበውም ጥናት ያልተጠናበት እና የክለቦችን ይሁንታ ያላገኘ በመሆኑ እንዲሁም ህዝብን ከህዝብ የሚለያይ በመሆኑ እንደሆነ ሰምተናል።በቀጣይ ሊጉ በምን መልኩ ይቀጥላል የሚለው ጉዳይ ክለቦቹ ተመካክረው እንዲወስኑ አቅጣጫ ተሰጥቷል።በዚህ ጉዳይ ላይ ዝርዝር መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን", "passage_id": "014ea9f021c909d10b483e3ad06bfe7e" }, { "passage": "የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ከሦስት ሳምንት በፊት በኳታር ዶሃ ባሳለፈው ውሳኔ ምስራቅ አፍሪካውያንን ቅር ያሰኘ ነበር። ዓለም አቀፍ ማህበሩ ከ2020 ጀምሮ የአምስት ሺ ሜትር ውድድር ከዳይመንድ ሊግ ፉክክር እንዲወጣ መወሰኑን ተከትሎ በርቀቱ ውጤታማ የሆኑት ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን ቅሬታቸውን በደብዳቤ ጭምር ሲገልፁ ቆይተዋል። ሁለቱ አገራት በጋራ በመቆም ውሳኔውን ለማስቀየር ጥረት እንደሚያደርጉም የስፖርት ቤተሰቡ ተስፋ አድርጓል። እነሱም በጋራ ውሳኔውን ለማስቀየር ቃል ገብተዋል። ባለፈው ቅዳሜ የዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና በዴንማርክ አርሁስ ከተማ ሲካሄድ የኢትዮጵያና ኬንያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች የስራ ኃላፊዎች በተናጠል የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የስራ ኃላፊዎችን በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግረዋል። ኬንያውያን ከውይይቱ በኋላ ውሳኔውን ከሌሎች አፍሪካውያን ጋር በጋራ በመሆን ከማስቀየር ይልቅ የዳይመንድ ሊጉን ለውጥ የተቀበሉት በሚመስል መልኩም ወላዋይ አቋም አሳይተዋል። የዓለም አቀፍ ማህበሩ ፕሬዚዳንት ሴባስቲ ያን ኮ እንዲሁም ዋና ጸሐፊው ጆን ሪድጎን ለኬንያውያን እንዳስረዱት በዳይመንድ ሊጉ ላይ የተደረገው ለውጥ አፍሪካውያንን አይጎዳም። ሪድጎን ለኬንያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሌተናል ኮሎኔል ጃክሰን ቱዌ የዳይመንድ ሊጉ ለውጥ በአፍሪካውያን ላይ ምንም አይነት ተፅዕኖ እንደሌለው ማሳመናቸውን ዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በድህረ ገፁ አስነብቧል። ሪድጎን በዳይመንድ ሊጉ ላይ የተደረገው ለውጥ ምስራቅ አፍሪካውያንን የ5ሺ ሜትር የውድድር እድል እንደማያሳጣም ለቱዌ ቃል መግባታቸው ታውቋል። ፕሬዚዳንቱ ኮ 5ሺ ሜትር ከዳይመንድ ሊግ የተሰረዘበትን ምክንያት አብራርተዋል። አዲሱ የውድድር ይዘት የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች በተለያዩ ከተሞች ሲካሄዱ ከቴሌቪዥን ስርጭት መብት ጋር በተያያዘ በእያንዳንዱ ከተማ የሚካሄደው ውድድር የዘጠና ደቂቃ ርዝመት ብቻ ይኖረዋል። 5ሺ ሜትር በዚህ ዘጠና ደቂቃ ውስጥ መካሄድ አይችልም። ይህ ማለት ግን በርቀቱ ከዘጠናው ደቂቃ ውጪ ውድድር አይደረግም ማለት አይደለም። በርካታ ከተሞችም ይህን የ5ሺ ሜትር ውድድር ለማዘጋጀት ፍቃደኝነታቸውን እያሳዩ እንደሚገኙ ፕሬዝዳንቱ አብራርተዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የገበያ ጥናት የዓለማችን ኮከብ አትሌቶች ጥራትና ተከታታይነት ያለው ፉክክር በዳይመንድ ሊግ ውድድሮች ማሳየት እንዳለባቸው የቴሌቪዥን ስርጭት ባለመብቶችና የስፖርቱ ደጋፊዎች ቅሬታ እንደሚያቀርቡ ሪድጎን ተናግረዋል። በተመሳሳይ የ5ሺ ሜትር ሯጮች፣አሰልጣኞችና ወኪሎች ዳይመንድ ሊጉ ላይ ለውጥ ሊደረግ ሲታሰብ ዓለም አቀፍ ማህበሩ አማክሯቸው በዓመቱ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች ስድስት ፉክክሮችን የማድረግ ፍላጎት እንደሌላቸው ማሳወቃቸውን ተናግረዋል። ባለፈው የውድድር ዓመትም ፈጣን ሰዓት ያላቸው ትልልቅ አትሌቶች በ5ሺ ሜትር ከሁለት ውድድር በላይ እንዳላደረጉ በምሳሌነት አስቀምጠዋል። በአዲሱ የዳይመንድ ሊግ ይዘት የመጨረሻው ረጅም የመወዳደሪያ ርቀት 3ሺ ሜትር የሆነውም ታላላቅ አትሌቶች ተከታታይ የሆኑ በርካታ ውድድሮችን በርቀቱ የመፎካከር የተሻለ ፍላጎት ስላላቸው መሆኑን አስረድተዋል። ከዚህ በተጨማሪ የረጅም ርቀት ሯጮች በአንድ የውድድር ዓመት በ3ሺ ሜትር የዳይመንድ ሊጉን ፍፃሜ ጨምሮ ሰባት ውድድሮችን እንዲሁም ተጨማሪ 5ሺ ሜትር ውድድር ማድረግ መቻላቸው የለውጡ መነሻ መሆኑን አብራርተዋል። አዲሱ የዳይመንድ ሊግ ይዘት ተግባራዊ በሚሆንበት 2020 መጨረሻ ላይ ግምገማ ተካሂዶም ማሻሻያዎችን ሊኖሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ሴባስቲያን ኮ በበኩላቸው ይህ የዳይመንድ ሊግ ለውጥ ምስራቅ አፍሪካውያንን ከመጉዳት ይልቅ እንደሚጠቅም በመናገር ለማሳመን ሞክ ረዋል። ለውጡ ምስራቅ አፍሪካውያንን ጨምሮ ሌሎች የዓለማችን ድንቅ አትሌቶች በአንድ ላይ የሚፎካከሩበት እድል ከመፍጠር ባሻገር ፉክክሮችን ጠንካራና ሳቢ እንዲሁም ከገበያ አኳያ ትርፋማ እንደሚያደርጋቸው ተናግረዋል። ዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የውድድር ዓመቱን መርሃግብሮች ከመከለስ አንስቶ ሌሎች የውድድር አማራጮችን ለማስፋት የሚያደርገው ጥረት እንዳለ ማስታወስም ጠቃሚ መሆኑን ኮ አብራርተዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የስራ ኃላፊዎች የሰጡትን ማብራሪያ ተከትሎ የኬንያው አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ቱዌ ‹‹አትሌቶቻችን በ2020 በቂ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እንደሚያገኙ ስሰማ ረክቻለው፣ ዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበርም ዳይመንድ ሊጉ ላይ በተፈጠረው ለውጥ ምክንያት የሚመጡ አሉታዊ ተፅዕኖዎች ካሉ ከአባል ፌዴሬሽኖች ጋር በመወያየት አስፈላጊው ማሻሻያ እንደሚደረግ ቃል ገብተዋል›› በማለት ተናግረዋል። ኬንያውያን ከዓለም አቀፉ ማህበር የስራ ኃላፊዎች ጋር ከተወያዩ በኋላ ውሳኔውን ለማስቀየር ያላቸው አቋም መለሳለሱ ያልተጠበቀ ቢሆንም ምንም ነገር መሬት ላይ ሳይወርድ በቃል ብቻ እንደተታለሉ የሚያሳይ ነው። በተለይም የዓለም አቀፍ ማህበሩ የዳይመንድ ሊጉ ለውጥ አፍሪካውያንን ከመጉዳት ይልቅ ጠቃሚ መሆኑን ያስረዱበት ሂደት አንድም ተጨባጭ ነገር የለውም። በ5ሺ ሜትር የውድድር አማራጮች ዳይመንድ ሊጉ ባይኖርም በርካታ እንደሆኑ ያስረዱበት መንገድም አሳማኝ አይደለም። የ5ሺ ሜትር ውድድሮችን ለማዘጋጀት በርካታ አገራት ፍላጎት ማሳየታቸውን የገለፁትም ነገ አትሌቶቻችን በርቀቱ በርካታ የውድድር አማራጭ እንደሚያገኙ የሚያስተማምን አይደለም። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የስራ ኃላፊዎች የውድድሮችን ህልውና ከመጠበቅ ይልቅ በገበያ ልማት ላይ ማተኮራቸውንም ኬንያውያንን ለማሳመን የሄዱበት መንገድ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።አዲስ ዘመን መጋቢት 26/2011 ", "passage_id": "54913d6c14a757ac1b8018dc10faa111" }, { "passage": "የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር የተላለፈበት ቅጣት ውሳኔ ተገቢ አይደለም በሚል ለፌዴሬሽኑ ይግባኝ ብሏል።ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአዳማ ከነማ ጋር ባደረገው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 14ኛ ሳምንት ጨዋታ ላይ በተፈጠረው ሁከት  ሁለቱም ክለቦች ጥፋተኛ ሆነው አግኝቻቸዋለው በማለት የዲሲፒሊን ኮሚቴው ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን በተለይ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ላይ ከበድ ያለ የቅጣት ውሳኔ ወስኗል ። ቅጣቱ ዝርዝር ነገሮች ቢኖሩበትም በዋናነት ቡድኑ በሜዳው የሚያደርገውን አንድ ጨዋታ በዝግ እንዲያደርግ እና የ180 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል ነው የተወሰነበት።ውሳኔውን ተከትሎ አንድ ጨዋታ በሜዳው ሲጫወት በዝግ እንዲሆን የተላለፈው ውሳኔ በየትኛው ጨዋታ ላይ እንደሆነ  ፌዴሬሽኑ በግልፅ አላስቀመጠም ። ይህ በመሆኑም ቅዱስ ጊዮርጊስ በቀጣይ በየትኛው ጨዋታ ላይ ቅጣቱ ተግባራዊ እንደሚሆንበት ማወቅ የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል። ይህንን ሀሳብ በመያዝ ሶከር ኢትዮጵያ የክለቡን አመራር በማናገር አጭር ምላሽ አግኝታለች። በምላሹም ክለቡ በውሳኔው ዙርያ ውይይት አድረጎ ዛሬ ለፌዴሬሽኑ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ይግባኝ እንዳቀረበ ተነግሮናል ።ክለቡ ይግባኝ የጠየቀ በመሆኑ በቀጣይ ኮሚቴው የሚያስተላልፈው ውሳኔ የሚጠበቅ ቢሆንም በ12ኛ ሳምንት የኢትዮዽያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ከነገ በስትያ ከደደቢት ጋር የሚያደርገውን ወሳኝ ጨዋታ በዝግ እንደማያደረግ መገመት ተችሏል ።", "passage_id": "77640aea442637db3ed508810f130005" }, { "passage": "የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በቻይና የሚካሄደውን የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር ማራዘሙን አስታወቀ። እአአ ከመጋቢት 13 እስከ 15 ቀን 2020 በቻይና ናጂንግ ከተማ ሊካሄድ የነበረው 18ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክውድድር ለ12 ወራት ያህል እንዲራዘም መደረጉን የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ዋቤ አድርጎ ቢቢሲ ዘግቧል። የዓለም አትሌቲክስ\nየጤና ቡድን ከዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ጋር በቻይናና ከቻይና ውጪ በሌሎች አገራት የኮሮኖ ቫይረስን አስመልክቶ በቅርበት መረጃዎችን\nበመለዋወጥ ባገኘው መረጃ ኮሮና ቫይረስ አሳሳቢ ደረጃ ላይ የሚገኝ እንደሆነ ለመረዳት መቻሉን ዘገባው አመልክቷል። በቻይና መነሻውን\nያደረገው ኮሮና ቫይረስ 130 ሰዎችን የገደለ ሲሆን፤ በ16 ሀገራት ተስፋፍቷል። ከስድስት ሺህ ሰዎች በላይም በቫይረሱ መጠቃታቸውን\nለማወቅ ተችሏል። ከዚህ በመነሳት የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቻይና በተስፋፋው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት ውድድሩን በተባለለት\nጊዜ ማካሄድ አስቸጋሪ መሆኑን በማመን ውድድሩ እንዲራዘም ውሳኔ አሳልፏል። በመሆኑም እ.አ.አ በ2021 ውድድሩ እንዲካሄድ አማራጭ\nመቅረቡን አስታውቋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል። የዓለም የቤት ውስጥ\nአትሌቲክስ ውድድሩን በሌሎች አገራት ለማድረግ አስቦ እንደነበር ያስታወቀው ፌዴሬሽኑ ቫይረሱ ከቻይና ውጪ ወደ ሌሎች አገራት የመሰራጨቱ\nጉዳይ አሳሳቢ ስለሚሆን አገር የመቀየር ምርጫውን መሰረዙን አመልክቷል። ብዙ አትሌቶች ውድድሩ እንዲካሄድ ካላቸው ፍላጎት አንጻርም\nየዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድሩን ሙሉ ለመሉ የመሰረዝ ምርጫውንም እንደተወውም ነው ተጠቀሰው። ይህ በመሆኑ ምክንያት ናንጂንግ\nእ.አ.አ በ2021 ውድድሩን የሚካሄድበት ምቹ ጊዜ ማግኘት እንደምትችል የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል። የዓለም አትሌቲክስ ከአትሌቶች፣\nከናንጂንግ የውድድር አዘጋጅ ኮሚቴና ከአጋሮች ጋር የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድር እ.አ.አ 2021 የሚካሄድበት ቀን ለመወሰን\nበቅርበት እንደሚሰራም አስታውቋል። የዓለም አትሌቲክስ\nቻይና የኮሮኖ ቫይረስን ለመከላከል እያደረገች ያለችውን ጥረት እየተከታተለ እንደሆነና ተቋሙ አገሪቷ እያከናወነች ላለው ሥራ ድጋፍ\nእንደሚያደርግም ቃል መግባቱንም አስፍሯል። ቫይረሱን አስመልክቶ ለአትሌቶች፣ ለብሔራዊ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖችና አጋሮች በፍጥነት\nእየተለዋወጡ ያሉ ጉዳዮችን ማሳወቅ ተገቢ እንደሆነም ማመልክቱን ቢቢሲ ዘግቧል። የእስያ አትሌቲክስ\nፌዴሬሽን በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በየካቲት ወር 2012 ዓ.ም በቻይና ሀንግዙ ግዛት ሊካሄድ የነበረውን ዘጠነኛው የእስያ የቤት\nውስጥ አትሌቲክስ ውድድር መሰረዙን ከአራት ቀናት በፊት ማስታወቁ ይታወሳል።አዲስ ዘመን አርብ ጥር 22/2012ዳነኤል ዘነበ ", "passage_id": "3a8f26005617a2af28416a8466fa1786" }, { "passage": " የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በቅርቡ ባስተላለፋቸው ውሳኔዎች ላይ ይግባኝ ለጠየቁ አካላት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት አዲስ ነጋሽ እገዳው ዝቅ ሲደረግለት በአርቢቴር ጌቱ ተፈራ እና ረዳቶቹ ላይ ተላልፎ የነበረወ ውየ6 ወራት እገዳ ተሽሯል፡፡ፌዴሬሽኑ ለሚድያ አካላት የላከው ፅሁፍ የሚከተለው ነው:-*በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ጥር 25 እና የካቲት 1 /2008 ያስተላለፋቸው ውሳኔዎች1. ታህሳስ 4 ቀን 2008 የቅዱስ ጊዮርጊስና ደደቢት የሴቶች እግር ኳስ ክለቦች በተጫወቱበት ወቅት ዋና ዳኛዋን ተማትታለች በማለት የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨዋች በሆነችው አትክልት አሸናፊ ላይ በዲሲፕሊን ኮሚቴ የተላለፈው የስድስት ወራት የጨዋታና የብር 5000 የቅጣት ውሳኔ ፀንቷል፡፡2. ታህሳስ 21 ቀን 2008 ዓ.ም በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እግር ኳስ ውድድር ዳሸን ቢራ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ክለቦች በተጫወቱበት ወቅት ኤሌክትሪክ ተጨዋች የሆነው አዲሱ ነጋሽ ዋና ዳኛውን በቦክስ በመማታቱና ምራቁንም ዳኛው ላይ በመትፋቱ በዲስፕሊን ኮሚቴ የተላላፈበት የብር 5000 የገንዘብ ቅጣት ጸንቷል፡፡ የአንድ ዓመት የቅጣት እገዳ ደግሞ ወደ ስምንት ወራት ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡*የኤሌክትሪክ ተጨዋች የሆነው አማረ በቀለ አራተኛ ዳኛውንና ታዛቢውን በመሳደቡ በዲስፕሊን ኮሚቴ የተላላፈበት የአራት ጨዋታ ቅጣት ጸንቷል፡፡*የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አሰልጣኝ የሆነው ብርሃኑ ባዩ ዋና ዳኛውንና ፌዴሬሽኑን ጸያፍ ስድብ በመሳደቡ በዲስፕሊን ኮሚቴ የተላለፈበት የ10 ጨዋታ ቅጣት እና የብር 5000 የገንዘብ ቅጣት ጸንቷል፡፡ክለቦቹ ለይግባኝ ያስያዙት ገንዘብም ለፌዴሬሽኑ ገቢ እንዲሆን ተወስኗል፡፡3. ታህሳስ 11 ቀን 2008 ዓ.ም በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የድሬዳዋ ከተማ እና ሃዲያ ሆሳዕና ክለቦች ካካሄዱት ጨዋታ ዳኝነት ጋር በተያያዘ ብሄራዊ የዳኞች ኮሜቴ በኮሚሽነር አሰፋ ንጉሴ ፣ በዋና ዳኛ ጌቱ ተፈራ እንዲሁም በረዳት ዳኛ ዳንኤል ዘለቀ ላይ ያስተላለፈው የስድስት ወራት የእገዳ ቅጣት ተሽሯል፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን", "passage_id": "24f57e9237e3e4b8c4d5625c16ab2125" } ]
81611d0b5ec7dcb6b33d588ca39c451e
c239e39f20c511ff08e70736ccc030da
ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሦስት ሳተላይቶችን ታመጥቃለች
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ለተለያየ አገልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን እንደምታመጥቅ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ እንደገለፁት፤ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ውስጥ ለተለያዩ አግልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን ለማምጠቅ ታቅዷል። በአሥር ዓመቱ ከሚመጥቁት ሳተላይቶች ውስጥ አንደኛው የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሲሆን፤ የተቀሩት ሁለቱ የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች ናቸው። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ፤ የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሳተላይት የሚባለው በብሮድካስት ሚዲያዎች ለኢንተርኔት፣ ለስክልና ለኮሚዩንኬሽን አገልግሎት የሚውል ነው። በአሁኑ ሰዓት ሀገራችን እነዚህን አገልግሎቶች ከውጭ በመከራየት በሚሊዮን ዶላር የሚገመት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ታወጣለች። ለአብነትም፣ ከብሮድካስቲንግ በዓመት እስከ አሥር ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደረጋል። ለቴሌ ኮሚዩንኬሽን ደግሞ በርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ወጭ ይሆናሉ። ስለዚህ ሳተላይት የመገንባት እቅዱን በተግባር በማረጋገጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪን መቀነስ ተገቢ ነው። ከኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሳተላይት በተጓዳኝ ሁለት የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች የሚገነቡ ሲሆን፤ በጥቅሉ በዚህ ዘርፍ የሚደረገው ልማት የህዝባችንን ኑሮ በማሻሻል ገቢውን ከማሳደግ አንጸር ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ሲሉ አቶ አብዲሳ ተናግረዋል። አቶ አብዲሳ እንደሚሉት፣ ቴክኖሎጂን ከማሳደግ ጎን ለጎን የሥራ እድል በመፍጠር ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬን ማስቀረት እና ዘርፉ የራሱ የገቢ ምንጭ ሆኖ የውጭ ምንዛሬ እንዲያስገኝ ለማድረግ ይሰራል። በዘርፉ የሚደረግ ልማት የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የሥራ እድል ለመፍጠር እና በየዘርፉ የታዩ ችግሮችን በስፔስ ሳይንስ ስኬታማ ስራዎችን በመስራት ሀገርን በሁሉም ዘርፍ ለማሳደግ መስራት ነው። በተለይም ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ በማስቀረት የስፔስ ሳይንስ ዘርፉ የውጪ ምንዛሬ የሚያገኝበትን መንገድ አላማ አድርጎ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለጹት፤ በ2011 ዓ.ም የወጣው ፖሊሲ በግልፅ እስንዳስቀመጠው ዘርፉ በራሱ ኢንዱስትሪ ሆኖ በመውጣት የሥራ እድል ለመፍጠርና በቀጣይ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ ዛሬ ላይ የሚሰራው ስራ እና በስፔስ ሳይንስ ውስጥ የሚኖረው ተሳትፎ ወሳኝ ነው። የቴክኖሎጂ አቅምን ከመገንባት አንፃር የሚሰራው ስራም ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ መተግበሪያዎችን ወደስራ በማስገባት የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል አቶ አብዲሳ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37690
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ያመጠቀቻት ሳተላይት ምድርን መቃኘት መጀመሯን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።ምድርን እየቃኘች እና በፎቶ እየመዘገበች መረጃ የምትሰበስበው “ETRSS-1” በዛሬው ዕለት ነበር ወደ ህዋ የመጠቀችው።ሳተላይቷ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናት እና ምርምሮችን ለመስራት እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ለማከናወን የሚያስችሉ መረጃዎችን ትልካለች ነው የተባለው።ሳተላይቷ በቻይና ከሚገኝ የማምጠቂያ ማዕከል ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች በተገኙበት ወደ ህዋ የመጠቀች ሲሆን፥ በአዲስ አበባ ውስጥም ይህን ታላቅ ታሪካዊ ክስተት የሚዘክሩ በርካታ ዝግጅቶች እየተከናወኑ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሳተላይቷ በዋናነት ግብርናውን ለማዘመን በእውቀትና በመረጃ ላይ በመንተራስ ስራዎችን ለመስራት የምታግዝ፣ በአፍሪካና በዓለም ገበያ በእውቀት ላይ በመመስረት ለመወዳደር እና ውጤታማ ለማድረግ ታስችላለች ብለዋል።", "passage_id": "7f1b552934ab3ed6fada8eec572cd2b8" }, { "passage": "የመሬት ምልከታ ሳተላይት መሬትን እየቃኘ መረጃዎችን በፎቶ ይመዘግባል\n\nሳተላይቱ ከምድር ወደ ህዋ ከተመነጠቀ በኋላ መሬትን እየቃኘ መረጃዎችን በፎቶ ይመዘግባል። እንደያስፈላጊነቱም መረጃውን ወደ ምድር ይልካል።\n\nአፍሪካ ውስጥ እስካሁን ሳተላይቱን ያመጠቁ በጣት የሚቆጠሩ ሀገሮች ናቸው። ኢትዮጵያም የአምጣቂዎቹን ቡድን ለመቀላቀል መሰናዶ የጀመረችው ከሁለት ዓመት በፊት ነበር።\n\nሳተላይቱን ሀገር ውስጥ ለመስራት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ለማምጠቅ የሚያስፈልገው ቴክኖሎጂና የሰው ሀይል ባለመኖሩ ወደ ሩቅ ምሥራቅ ስታማትር፤ ቻይና የገንዘብና የሙያም እገዛ ለመስጠት ተስማማች።\n\n• ኦነግ እና መንግሥትን ለማግባባት የሃገር ሽማግሌዎች እየጣሩ ነው\n\n• ትራምፕ ጠቅላይ አቃቢ ሕጉን አባረሩ \n\nከቻይና 6 ሚሊየን ዶላር ተለግሶ ስራው ተጀመረ። ቻይናውያን ኢንጂነሮች ኢዮጵያውያንን እያሰለጠኑ ሳተላይቱ ቻይና ውስጥ እንዲሁም በከፊል ኢትዮጵያ ውስጥ ተገነባ።\n\n70 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ሳተላይት በ2012 ዓ. ም. መባቻ ላይ ከቻይና ይመጥቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሰለሞን በላይ ለቢቢሲ ተናግረዋል።\n\nሳተላይቱ በቻይና እገዛ ከምድረ ቻይና ይምጠቅ እንጂ፤ \"ተቆጣጣሪዋም፣ አዛዧም ኢትዮጵያ ናት\" የሚለውን አስምረውበታል።\n\nሳተላይት ማምጠቅ ለምን አስፈለገ?\n\nየህዋ ጥናት በዓለም ላይ በፍጥነት እየዘመኑ ካሉ ዘርፎች መካከል ይጠቀሳል። የሰው ልጅ ምድር ጠባው አልያም ከምንኖርበት ዓለም ውጪ ያለውን ለማወቅ ጓጉቶ ዘወትር እየቆፈረ ነው።\n\nከህዋ ፍተሻ በተጨማሪ ህዋን ተጠቅሞ መሬትን ማሰስ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ተግባር ነው። ሳተላይቱ መረጃ ሲሰበስብ ይህ ቀረህ አይባለውም። ከግዙፍ ክንውኖች እስከ ጥቃቅን እንቅስቃሴዎች ይመዘግባል።\n\nእንደ ባለሙያዎች አባባል ሳተላይቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው። የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ የተፈጥሮ አደጋዎች ከመድረሳቸው አስቀድሞ ለመተንበይ፣ ደህንነትን ለመጠበቅ ወዘተርፈ ይውላል።\n\nበእርግጥ ብዙዎች በታዳጊ ሀገር የህዋ ጥናት አስፈላጊነቱ ላይ ጥያቄ ቢያነሱም፤ ዶ/ር ሰለሞን \"ህዋ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገሮች የመኖርና ያለመኖር ጥያቄ ነው፤ ቅንጦት አይደለም\" ይላሉ።\n\nየአየር ንብረት ለውጥ የመላው ዓለም ስጋት በሆነበት ዘመን፤ አንዳች ተፈጥሯዊ አደጋ ከመድረሱ በፊት አስቀድሞ መረጃ ማግኘት ብልህነት ነው።\n\nየዛፍ ቁጥር፣ የአየር ንብረት ለውጥና ሌሎችም መረጃዎች ከተሰበቡ በኋላ እንደ ጎርፍ ያሉ አደጋዎች ከመከሰታቸው በፊት መተንበይ ይቻላል።\n\n• ግጭትን ለማባባስ ፌስቡክ ጥቅም ላይ ውሏል ተባለ \n\n• በቤታችን ውስጥ ያለ አየር የጤናችን ጠንቅ እንዳይሆን ማድረግ ያለብን ነገሮች \n\nግብርና ቀዳሚ መተዳደሪያ በሆነባት ሀገር የቱ አካባቢ ምርታማ ነው? የአየር ንብረት ለውጥ ይኖር ይሆን? የሚሉ ጥያቄዎች በቀላሉ እንዲመለሱ የሳተላይቱ መረጃ አስፈላጊ ይሆናል።\n\nዶ/ር ሰለሞን እንደሚሉት፤ አንድ የግብርና አካባቢን የሚያሳይ ፎቶግራፍ ስለ እርሻ መሬቱ፣ ስለ ውሀው፣ ስለ አፈሩ ዝርዘር መረጃ ይሰጣል። መረጃዎቹን በመጠቀም ምርታማ የሆኑ አካባቢዎችን መለየት፣ የምርት መጠንን በትክክል ማወቅም ይቻላል።\n\nኢንዱስትሪዎች እየተስፋፉ በመጡባት ኢትዮጵያ፤ ፋብሪካዎች የት መገንባት አለባቸው? ለሚለው ጥያቄ የሳተላይቱ መረጃ መልስ ሊሰጥ ይችላል።\n\nሕዝብ መቁጠር ሲያስፈልግ ከዘልማዳዊው መንገድ ሳተላይቱን መጠቀም ይመረጣል። ትክክለኛ መረጃ ከማግኘት፣ ገንዘብና የሰው ሀይል ከማዳን አንጻርም የተሻለው አማራጭ ነው።\n\nሳተላይቱን ደህንነትን ከመጠበቅ ጋር የሚያስተሳስሩት ባለሙያዎች አሉ። ዶ/ር ሰለሞን በበኩላቸው \"በመርህ ደረጃ ህዋ የሚውለው... ", "passage_id": "1b21984c8635629b34f30a6e5c3579e0" }, { "passage": "በቻይና ድጋፍ ወደ ጠፈር የተላከችው የዚህች ሁለተኛ ሳተላይት ሥራ የመሬት ምልከታ መረጃ ማሰባሰብና ወደ ምድር ጣቢያ መላክ መሆኑን የኢትዮጵያ የጠፈር ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩትአስታውቋል።ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ETRSS-1 የተባለች የመጀመሪያዋን ሳተላይት ባለፈው ዓመት ታኅሣስ 2012 ዓ.ም ማምጠቋ ይታወሳል።“ETRSS-1” መሬትን እየቃኘችና በፎቶ የተደገፉ መረጃዎችን እየላከች መሆኗን የጠፈር ሳይንስ እናቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ይሽሩን ዓለሙ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።ሳተላይቷ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር የሚደረጉ ጥረቶችን ለማግዝ፣ ከግብርና ጋር የተያያዙጥናትና ምርምሮችን ለማከናወንና ሌሎች ለመሠረተ ልማት አገልግሎት የሚውሉ መረጃዎችንበማሰባሰብ ላይ ስትሆ ትናንት የመጠቀችው ET-Smart-RSSም ከቀድሞዋ ETRSS1 ጋር ተመሳሳይ ተልዕኮእንዳላት ዶ/ር ይሽሩን ተናግረዋል።(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)\n ", "passage_id": "660112559b447e03d80951ca6a1f68b6" }, { "passage": "እ.ኤ.አ. በጥቅምት 2015 በተፈረመ ስምምነት መሠረት ዕውን ሆና በቻይና መንግሥት በስምንት ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ዓርብ ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ወደ ህዋ የመጠቀችው ሳተላይት፣ ለኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንደምታስገኝ ተገለጸ፡፡ ይህች 72 ኪሎ ግራም የምትመዝነው የመሬት ምልከታ ሳተላይት በሰሜን ቻይና ከተማ ሻንግዚ ግዛት ከሚገኘው የታዩአን ሳተላይት ማስወንጨፊያ ጣቢያ ሎንግ ማርች ፎር ቢ (Long March 4B) በተባለ ሮኬት ተሸካሚነት ወደ ህዋ መጥቃለች፡፡ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናትና ምርምሮች ለማካሄድና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎችን ለማከናወን ታስችላለች ተብሏል፡፡ በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ የኮሙዩኒኬሽንና የብሮድካስት ሳተላይት ለማምጠቅ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ከቻይና ወደ ህዋ የመጠቀችው ሳተላይት በአጠቃላይ ግንባታዋ ከንድፍ አንስቶ ሁለት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን፣ በንድፍና በግንባታ ሒደት 21 ኢትዮጵያውያን የሥልጠና ተሳትፎ አድርገውበታል፡፡ “ETRSS-1” የሚል መጠሪያ የተሰጣት ሳተላይት የመጠቀችው ከቻይና ቢሆንም፣ የሳተላይቱ የመቆጣጠሪያና የአንቴና ክፍሎች ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው የሚገኘው መረጃ ለግብርና፣ ለአደጋ መከላከልና ለመሳሰሉ ጉዳዮች ጥቅም ላይ እንደሚውል ተገልጿል፡፡ በአፍሪካ እስካሁን ሰባት አገሮች ብቻ ሳተላይት ያመጠቁ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ሳተላይት በማምጠቅም ከአኅጉሪቱ ስምንተኛ ሥፍራን ይዛለች፡፡ ይህች ሳተላይትም በቀጥታ ከምትሰጠው ጠቀሜታ ባለፈም የቴክኖሎጂ አቅምን በመገንባት፣ የወደፊት የሳተላይት ግንባታንና ማምጠቅን በራስ አቅም ማከናወን የሚያስችል ጠቀሜታ ይኖራታል ተብሏል፡፡ ከዚህ አኳያም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክና ኤርያል ከተባለ ተቋም ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የሳተላይት መገጣጠሚያና መሞከሪያ ጣቢያ ለመገንባት በትብብር እየሠሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡ የዚህ ፕሮጀክት የአዋጭነት ጥናት ከኅዳር 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ሲከናወን እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል፡፡ የአሁኑ ሳተላይት ማምጠቅ ከሲቪል ጠቀሜታዎች ባለፈም ኢትዮጵያ በሒደት ልትገነባው ለምታስበው የህዋ መከላከያ ኃይል በር ከፋች ሊሆን እንደሚችል አስተያየት ሰጪዎች ይጠቁማሉ፡፡ በዓለም የጦርነት ዓውዶች ከተለመደው ወጣ በማለት ወደ ሳይበርና ወደ ህዋ እየተቀየሩ ስለሆነ፣ በዚህ ዘርፍ ጠንካራ የመከላከል አቅምን መገንባት አስፈላጊ እንደሆነ በማተት፣ የህዋ መከላከያ ክፍል በአገር መከላከያ ሠራዊት እንደሚቋቋም ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከዚህ ቀደም ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ ከዚህ ፍላጎት ጋር በሚመጋገብ ሁኔታ የዛሬ ዓመት ገደማ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር)፣ ከቻይና የስፔስና የሳይበር ደኅንነት ተቋም ጋር የትብብር ውይይት አድርገው ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ሳተላይት ወደ ህዋ ከመጠቀች ከሦስት እስከ አምስት ባሉ ቀናት ምህዋሯን ይዛ መረጃዎችን ከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት ባለው ካሜራ ፎቶ እያነሳች ወደ ዕንጦጦ መቀበያ ማዕከል መላክ ትጀምራለች ተብሏል፡፡ ሳተላይቷ በቻይና ቁጥጥር ሥር ሆና መረጃ ወደ ዕንጦጦ ማዕከል መላኳ በአንዳንዶች ዘንድ ሥጋት ቢፈጥርም፣ አቅምን መገንባት እስከሚቻል ድረስ በሳተላይቷ መጠቀም አማራጭ የለውም የሚሉ ድምፆች ተሰምተዋል፡፡የሳተላይቶች ዋጋና መጠን እያነሰ በመጣ ቁጥር በርካታ አገሮች ሳተላይት የማምጠቅ ፍላጎታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ እንደ ኬንያ፣ ናይጄሪያ፣ ግብፅ፣ ደቡብ አፍሪካና ሞሮኮ ከተለያዩ አካላት ጋር በመተባበር ያመጠቁና ለማምጠቅ በዝግጅት ላይ ካሉ አገሮች ተርታ ይገኛሉ፡፡ ይኼ ፍላጎትም በአፍሪካ ኅብረት የስፔስ ፖሊሲ የሚደገፍ ሲሆን፣ የሳተላይት ግንኙነቶችን ለኢኮኖሚ ልማት መጠቀምን በእጅጉ ያበረታታል፡፡ የሳተላይቷን ጠቀሜታ በሚመለከት ለሪፖርተር አስተያየታቸውን የሰጡት ዚነሲስ ቴክኖሎጂስ የተባለው የመረጃ ትንታኔ ላይ የሚያተኩር ድርጅት የኢትዮጵያ ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ካሳ፣ ‹‹የETRSS-1 ሳተላይት መምጠቅ ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ነው፤›› ብለው፣ በተለይም ከመረጃ (Data) አኳያ ትልቅ ዕርምጃ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቶ ዳዊት እንደሚሉት ሳተላይቷ ለኢትዮጵያ በአየር ንብረት፣ በደን ሀብትና በተለያዩ ዘርፎች ቀዳማዊ መረጃን በመሰብሰብ የግብርና ዘርፉን ለማሳደግ ታግዛለች፡፡ ‹‹አዲሱ መረጃ ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ለነበራት መረጃ ትልቅ ጭማሪ ነው የሚሆነው፡፡ መረጃ ደግሞ ኃይል ነው፡፡ የወቅቱ ነዳጅ መረጃ ነው፡፡ ስለዚህም ‘ETRSS-1’ ኢትዮጵያ ካላት መረጃ ጋር በማጣመር የግብርና ዘርፏን ለማሳደግ፣ ለግብርና ፖሊሲ ቀረፃና ለድርቅ ቅድመ ትንበያ የሚረዱ መረጃዎችን ለማመንጨት ታግዛለች የሚል ትልቅ ተስፋ አለኝ፤›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ይኼም ለአካባቢ ጥበቃና ለአደጋ ጊዜ ፈጣን ምላሾችን ለመስጠት አጋዥ ነውም ብለዋል፡፡ ‹‹ይኼ ለኢትዮጵያ እጅግ ደስ የሚያሰኝ ጥሩ ቀን ነው፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡ የህዋ ሳይንሱ እንደ አንድ ቴክኖሎጂ ብቻ የሚታይ ጉዳይ አይደለም በማለት ጠቀሜታውን አጉልተው የሚያስረዱት ደግሞ፣ የኢትዮጵያ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዱቃን ደበበ ናቸው፡፡ ሳተላይት ለኢትዮጵያ አሁን ጊዜው እንዳልሆነ በመጥቀስ ዳቦ ይቅደም የሚሉ እንዳሉ በማንሳት የሚከራከሩ እንዳሉ የሚናገሩት አቶ ሳንዱቃን፣ ‹‹አሁን ከሰባት ሺሕ በላይ ሳተላይቶች በህዋ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሳተላይት ደግሞ እ.ኤ.አ. በ2019 ከተመሳሳይ ሥፍራ ከተወነጨፉ ሳተላይቶች 99ኛው ነው፡፡ ቁጥሮች የሚያሳዩት እንዲያውም መዘግየታችንን ነው፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹ሳተላይቱ በመጨረሻ ለዳቦና ለጤና ነው ጥቅም ላይ የሚውለው፤›› ብለው፣ ‹‹ከዚህ በተጨማሪም ቴክኖሎጂው ጠቃሚ እስከሆነ ድረስ መቅደም ወይም እኩል መሄድ ነው ያለብን እንጂ ለምን እንዘግይ?›› ሲሉም ይጠይቃሉ፡፡ ‹‹በቆየን ቁጥር የሳተላይት መቀመጫ ምህዋር በሳተላይቶች ብዛት ስለማይኖር ዕድሎችን ሊያጠብብን ይችላል፤›› ሲሉም ያስረዳሉ፡፡እንደ ኢትዮጵያ ላሉ በግብርና ላይ የተሰማራ ሕዝብ ቁጥር ከ80 በመቶ በላይ በሆነበት አገር የአየር ንብረት ሁኔታን፣ የጎርፍ፣ የእሳተ ጎሞራ፣ እንዲሁም የአውሎ ንፋስ ሁኔታዎችን መከታተልና ማወቅ አስፈላጊ በመሆኑ፣ ቀድሞ የአየር ሁኔታውንና የሙቀት መጠኑን መረዳት እጅግ ጠቃሚ ነው መሆኑን አቶ ሳንዱቃን ያስረዳሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የከተማ ልማት፣ የመሬት አስተዳደር፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የደኅንነትና የመሳሰሉ ዘርፎችን በእጅጉ የሚደግፍ ጠቀሜታ ያለው የመሬት ቅኝት ሳተላይት እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ ", "passage_id": "6c090df0e95ff125943b6a3c68d8dd58" }, { "passage": "ኢትዮጵያ የሳተላይት መቆጣጠሪያ እና መረጃ መቀበያ ጣቢያ በእንጦጦ ኦብዘረቫቶሪና ምርምር ማዕከል ውስጥ እየገነባች ሲሆን የመሬት ምልከታ ሳተላይት መቀበያ አንቴናም ዛሬ ኅዳር 19/2012 ተገንብቶ ተጠናቋል። የኢትዮጵያ የህዋ ሳይንስ ቴክሎጂ ኢኒስቲቲዩት እንዳስታወቀውተገንብቶ የተጠናቀቀው ሳተላይት መረጃ መቀበያ አንቴና በመጪው ወር ታኅሳስ 1/2012 ወደ ህዋ ኢትዮጵያ የምታመጥቀውን ሳተላይት መረጃ ለመቀበል እንደሚረዳ አስረድቷል። ጣቢያው መረጃዎችን ከመቀበል ባለፈ ሳተላይቶች በአግባቡ ተልዕኳቸውን መፈፀማቸውን ክትትል የሚደረግበት፣ የሳተላይቶች ደህንነትና እንቅስቃሴንም ቁጥጥር የሚደረግበት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የእንጦጦ የሳተላይት መቆጣጠሪያ እና መረጃ መቀበያ ጣቢያ ፕሮጀክት ከተለያዩ ሳተላይቶች መረጃ መቀበል የሚያሥችል አንቴናና መረጃዎች የሚተነተኑበት የመረጃ ማዕከል ግንባታም እያከናወነ ይገኛል፡፡\nኢትዮጵያ የሳተላይት መረጃ ፍላጎቷን በከፍተኛ ወጪ የምታገኝ ሲሆን ፤ ይህንን በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለግዢ የሚወጣ የአገር ሃብት ለማዳን ያስችላል፡፡የጣቢያው መገንባት በአገር ውስጥና በአጎራባች አገራት ለሚገኙ የሳተላይት መረጃ ተጠቃሚዎች የመረጃ አገልግሎቱን በመሸጥ ገቢ ማስገኘትም እንደሚያስችል ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል፡፡", "passage_id": "151b96808a88d8562cb67b7ee0c113ad" } ]
2c5785c1d453295bafd398ebcd771172
4718f2a62c6baf81adfd79767ed4c4a3
‹‹ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ካልቻልን ራሴን አገላለሁ››
የኢትዮጵያ ሴት ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛውና የብሔራዊ ቡድኑ አምበል ብርቱካን ገብረክርስቶስ ከትናንት በስቲያ ከሰዓት በኋላ በኢትዮጵያ ሆቴል አጠቃላይ ስለ ብሔራዊ ቡድኑ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የሉሲዎቹ አዲስ አሰልጣኝ ብርሃኑ ‹‹እቅዴ ለ2020 የአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ነው፣ ይህን ማሳካት የማልችል ከሆነ በራሴ ፍቃድ ከኃላፊነት እራሴን አገላለሁ››በማለት በጋዜጣዊ መግለጫው ተናግሯል፡፡ አሰልጣኙ ቀደሞ የነበሩ አሰልጣኞች በቡድኑ የሰሩትን መልካም ስራ በማጠናከርና የጎደለው በመሙላት ስህተቱን አርሞ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ የሚችል ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን የመገንባት ፍላጎት እንዳለው አብራርቷል፡፡ አሰልጣኝ ብርሃኑ ሉሲዎቹን ለመምራት ከፌዴሬሽኑ የተሰጠው የስራ ውል ለሦስት ወራት ብቻ የሚዘልቅ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ በ2020 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች፣ በምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ(ሴካፋ) ውድድር በሚያስመዘግበው ውጤት መሰረት ውሉ የሚታደስ ይሆናል፡፡ ያም ሆኖ በአፍሪካ ዋንጫው ቡድኑን ማሳለፍ ካልቻለ ‹‹በእጄ ፈርሜ እንደገባሁ ፈርሜ ለመውጣት ዝግጁ ነኝ›› ብሏል። ከምስራቅና መካከለኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ጋር ተያይዞ አሰልጣኙ ቡድኑን ለማዘጋጀት ያለው ጊዜ አጭር መሆኑን በመግለፅ ተጫዋቾቹ ከእረፍት እንደመምጣታቸው ከፍተኛ የአካል ብቃት ችግር እንደተስተዋለባቸው ተናግሯል፡፡ በአሁን ወቅት አሰልጣኙና ረዳቶቹ መስራት የሚችሉት ነገር ተጫዋቾቹ በሜዳ ላይ የተሻለ ቅንጅት እንዲፈጥሩና ያላቸውን አቅም አውጥተው መጠቀም የሚችሉበትን ነገር መፍጠር መሆኑን አብራርቷል፡፡ ‹‹በሴካፋው ይህን ውጤት አመጣለሁ ብዬ መናገር የምንችልበት ነገር የለም፣ ውጤት ብናመጣም ባናመጣም ብዙም የሚያስከፋም የሚያስጨፍርም ነገር የለም፣ እኛ እቅዳችን የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ ነው፣ የሴካፋን ውድድር የብሔራዊ ቡድናችንን እንቅስቃሴ የምናይበትና ችግራችንን እያረምን የምንሄድበት ነው›› ሲልም አክሏል፡፡ አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው ከፌዴሬሽኑ የሚደረግለት ድጋፍ ጥሩ መሆኑን በመግለፅ ቡድኑ የጎደለበት ነገር እንደሌለና ይህም ከፍተኛ ለውጥ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን አሰልጣኙ ከፌዴሬሽኑ ጋር እንደማይስማማ ሲነሳ ስለነበረው ሃሳብ አሰልጣኙ ምላሽ ሲሰጥ ‹‹ፌዴሬሽኑ የኔን ሃሳብ በበጎ እንጂ በመጥፎ አልተመለከተውም፣ ለ18 ዓመት በሴቶች እግር ኳስ በውድድር ውስጥ አሳልፌያለሁ ብዙ ውጣ ውረዶችን ፣ አስቸጋሪ ጊዚያቶችን አሳልፌያለሁ የሴቶች እግር ኳስ ለኔ ደሜ ነው ለፍቼበታለሁ የማነሳው ሃሳብ ለውጥ እንዲመጣ እንጂ ለመጥፎ አይደለም›› ሲል ገልጿል። የብሔራዊ ቡድኑ አምበል ብርቱካን ገብረክርስቶስ በበኩሏ ቡድኑ የአንድ ሳምንት ዝግጅት ማድረጉን ገልፃ፣ በሜዳ ላይም ከሜዳ ውጪም ትምህርት መውሰዳቸውን አብራርታለች፡፡ ‹‹ በአሰልጣኞቻችን ጥሩ ስልጠና እየተሰጠን ነው፣ ጥሩ መነሳሳት ላይ እንገኛለን፣ እኔ ከበርካታ አሰልጣኞች ጋር ጥሩም መጥፎም ጊዜ አሳልፌያለሁ፣ አሁን ካለፈው ተምረን በመከባበርና ድክመታችን ላይ በመስራት ተደጋግፈን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለመግባት ነው እቅዳችን›› ብላለች። ሉሲዎቹ ትናንት ጠዋት ከ15 ዓመት በታች ወንድ ቡድኖች ጋር የመጨረሻ የወዳጅነት ጨዋታውን ያደረጉ ሲሆን ዛሬ ወደ ታንዛኒያ ያቀናሉ። በታንዛኒያ አዘጋጅነት የሚካሄደው የሴቶች ሴካፋ ዋንጫ ሕዳር ስድስት የሚጀምር ሲሆን ኢትዮጵያ በውድድሩ ከኬኒያ፣ ዩጋንዳና ጅቡቲ ጋር መደልደሏ ይታወቃል፡፡ የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ በምድብ ‹‹ሀ›› ታንዛኒያ፣ ብሩንዲ፣ ዛንዚባርና ደቡብ ሱዳን ተደልድለዋል፡፡ በምድብ ‹‹ለ›› ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ኢትዮጵያና ጅቡቲ ይገናኛሉ፡፡ በቻማዚ ስታዲየም በሚደረገው ውድድር ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ጨዋታ ከኬንያ ጋር ታደርጋለች፡፡ አዲስ ዘመን ጥቅም3/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22445
[ { "passage": "የፋሲል ከነማው አሰልጣኝ ሥዩም ከበደ ለኮንፌፌሬሽን ዋንጫ ቅድመ ማጣርያ ጨዋታ ቡድናቸው ስላደረገው ዝግጅት፣ የቡድኑ ወቅታዊ ሁኔታ እና ተያያዥ ጉዳዮች ወደ ቱኒዚያ ከማምራታቸው በፊት ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር አጠር ያለ ቆይታ አድርገዋል።ስለ ዝግጅት ጎንደር ላይ ነው ዝግጅት የጀመርነው። ከጎንደር የተሳካ የዝግጅት ጊዜ በኋላ ወደ አዲስ አበባ አቅንተን ብሔራዊ ቡድን ላይ የነበሩ ልጆችን በመቀላቀል ዝግጅታችንን ቀጥለናል። እንደ ቡድን ያለንበት ሁኔታ ምን ይመስላል የሚለውን ለማየት የወዳጅነት ጨዋታ ማግኘት ነበረብን። ከወልቂጤ ከነማ ጋር ተነጋግረን መጫወት ችለናል። በአጠቃላይ ነባሮቹ፣ ብሔራዊ ቡድን ላይ የነበሩት እና አዲስ ያመጣናቸውን አንድ ላይ ተቀላቅለው እንደ ቡድን የሆነ ነገር ለማየት ችለናል። እንግዲህ በዚህ ደረጃ ነው ለውድድሩ የተዘጋጀነው።ጉዳት እና ተያያዥ መረጃበቡድናችን ውስጥ ምንም አይነት የጉዳት ዜና የለም። በተጨማሪም ሁሉም ከኮቪድ 19 ነፃ ናቸው። ለጨዋታው ሙሉ ስብስቡ ዝግጁ ነው ።አላማወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍን አስበን ነው እየተዘጋጀን ያለነው። ከሜዳ ውጪ በምናደርገው ጨዋታ ለማሸነፍ የሚያስችለን ነገር ሁሉ ነው አቅደን የተዘጋጀነው። ያ ካልሆነ ደግሞ አቻ ወጥተን ወይም ለመልሱ ጨዋታ ልንገለብጠው የምንችለው ውጤት ይዘን ለመምጣት እየሰራን ነው ያለነው። ፍላጎታችንም እቅዳችንም በዛ መልክ ነው።የመልስ ጨዋታ…የመልሱ ጨዋታ አዲስ አበባ የሚደረግ ይመስለኛል። ሌላ አማራጭ ያለ አይመስለኝም።© ሶከር ኢትዮጵያ", "passage_id": "1e4f72431fb2d6cfb842cf06b0be8f89" }, { "passage": "ጨዋታው እንዴት ነበር ?ጠንካራ ጨዋታ እንደሚሆን እናውቃለን፡፡ ሰንዳውስ የአምና የአፍሪካ ቻምፕዮን የነበረና በሊጉም ሁለተኛ ደረጃ የሚገኝ ቡድን እንደመሆኑ ጠንካራ ፉክክር እንደሚኖር እናስባለን፡፡ ሆኖም ሁላችንም እያንዳዱ ተጨዋች ጋር ከፍተኛ የሆነ የማሸነፍ ፍላጎት ነበር። ጨዋታውንም እንዳያችሁት ከፍተኛ የሆነ አልሸነፍ ባይነት ትግል ነበር ፤  እያንዳንዱ ተጫዋች ታሪክ ሰርቶ ማለፍ ይፈልጋል። ምድብ ድልድል ውስጥ በመግባት አንድ ታሪክ ሰርተናል፡፡ አሁን ደግሞ ሩብ ፍፃሜ ውስጥ በመግባት ሁለተኛ ታሪክ ለመስራት ነው የምናስበው።ከጨዋታው በፊት አቅዳቹ የነበረው ምንድነው? እሱንስ አሳክተናል ትላላቹ ?ጨዋታውን በጥንቃቄ ተጫውተን አሸንፈን መውጣት እንዳለብን ተነጋግረናል ነው ወደ ሜዳ የገባነው። ሜዳው ውስጥም በየቦታቸው ይጫወቱ የነበሩት ተጨዋቾች በሙሉ በሚገርም አይነት የቡድን መንፈስ ነበር ሲጫወቱ የነበረው። እስከ ጨዋታው ፍፃሜ ድረስ ታግለን ቢያንስ ከሜዳ ውጭ እንደመጫወታችን የአቻ ውጤቱን አስጠብቀን ወጥተናል።በስታድየሙ ለተገኙት ደጋፊዎች ምን ማለት ይቻላል?በጣም ደስ ይል ነበር አዲስ አበባ ያለን ነበር የሚመስለው። ገና ከኤርፖርት ከገባንበት ጊዜ ጀምሮ ነበር የተቀበሉን ። ሆቴልም እየመጡ አብረውን በመሆን አይዟቹ ምን እናግዝ በማለት ይጠይቁን ነበር። ትላንትም እንዳያችሁት በርካታ ደጋፊዎች ነበሩ፡፡ እንዲያውም የእነሱ ደጋፊ አልነበሩም ማለት ይቻላል። ደጋፊዎቻችንም ለእኛ ትልቅ አቅም ነው የሆኑን፡፡ እንደ አምበልነቴ በዚህ አጋጣሚ በቡድኔ ስም ከጎናችን በመሆን ላበረታቱን ደጋፊዎች በሙሉ ምስጋናዬን አቀርባለው።በቀጣይ ጨዋታዎች ምን እንጠብቅ ?ከዚህ በኋላ ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች በሜዳችን እና በደጋፊያችን ፊት እንጫወታለን፡፡ ያው ለሁሉም ጨዋታዎች እኩል ግምት ነው የምንሰጠው ከፍፍለን የምናየው ጨዋታ የለም። ለዚህ ቡድን እንዲህ ብለን አንዘጋጅም፡፡ በቀሩት ጨዋታዎች ሁሉ ታሪክ ለመስራት ያለንን አቅም ለመስጠት ዝግጁ ነን ።", "passage_id": "6a3a36f1543e596c697a4ff265b2cffa" }, { "passage": "የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ይዘጋጅ የነበረው በወርሃ ሰኔ እና ሐምሌ ላይ የነበረ ሲሆን፤ ግን እነዚህ ወራት በካሜሩን ዝናባማ ስለሚሆኑ ወደ ጥር እንዲዘዋወር ተደርጓል ተብሏል። \n\nይህ ማለት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሚጫወቱ እና ለአፍሪካ ዋንጫ የሚያልፉ ሃገራት ተጫዋቾች እስከ ስድስት የክለብ ጨዋታ ያመልጣቸዋል።\n\nትናንት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን-ካፍ እና የካሜሮን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያካሄዱትን ስብሰባ ተከትሎ የካፍ ፕሬዝደንት በትዊተር ገጻቸው ላይ \"የ2021 የአፍሪካ ዋንጫ ከጥር 1 እስከ ጥር 29 ድረስ ይካሄዳል። የጊዜ ለውጡ በአየር ጠባይ ምክንያት በካሜሮን ጥያቄ መሠረት ተቀይሯል\" ሲሉ አስፍረዋል። \n\nየካፍ ምክትል ፕሬዚደንት ቶንይ ባፉኤ በበኩላቸው፤ በቀን ለውጡ ላይ ከካሜሮን ሜትዮሮሎጂ ባለሥልጣናት፣ አሰልጣኞች እና ተጫዋቾች ጋር እንዲሁም የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ ጋር በጥልቅ መወያየታቸውን አስረድተዋል። \n\nካሜሮን የ2019 ዋንጫን እንድታዘጋጅ ተመርጣ እንደነበረ ይታወሳል። ይሁን እንጂ ከስታዲየም ግንባታ እና ከአጠቃላይ ዝግጅት ጋር ተያይዞ የነበራት ዝግጁነት ዘገምተኛ ነው ከተባለ በኋላ ነበር ግብጽ እንድታዘጋጅ እድሉ የተሰጣት።\n\n• «የኔ ትውልድ ታሪክ እንደሚሠራ እምነት አለኝ» ሎዛ አበራ \n\n ", "passage_id": "8e407b55368045424831053f1c05a432" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሦስት አሥርት ዓመታት በኃላ የሰማይ ያህል ርቆ የቆየውን አፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ ያሳካበት ታሪካዊ ቀን ዛሬ ስምንት ዓመት ደፍኗል። ሁኔታውም በወቅቱ አንበል ደጉ ደበበ አንደበት እንዲህ ይገለፃል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሱዳን ላይ የደረሰበትን የ5-3 ሽንፈት ቀልብሶ ወደ 2013 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ አዲስ አበባ ላይ ህዝቡ እና ብሔራዊ ቡድኑ ዝግጅት ላይ ነው። ተመልካቹ እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2005 በጉጉት የሚጠበቀውን ይህንን ጨዋታ ለመመልከት አላስችል ቢለው እሑድ ለሚካሔድ ጨዋታ ዕለተ ቅዳሜን ስታዲየም ዙሪያ ሰልፍ ይዞ ብርድ ላይ ማደርን ምርጫው አድርጓል።ጨዋታው ተጀምሮ የመጀመርያው አጋማሽ ያለ ጎል መጠናቀቁ እና ቡድኑ ግልፅ የጎል ማስቆጠር አጋጣሚ ለመፍጠር መቸገሩ በስታዲየሙ የተገኘው እና በቤቱ ሆኖ በቴሌቭዥን የሚከታለው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተመልካችን አስጨንቋል። በሁለተኛው አጋማሽ ተሻሽለው በመግባት ተጋድሎ ያደረጉት ዋልያዎቹ በአዳነ ግርማ ጎል ቀዳሚ መሆን ቻሉ። በዚህች ጎል የተነቃቁት ዋልያዎቹ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የግድ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋቸው ነበር። በዚህ ሰዓት ነበር ወርቃማ ጎሏን ሳላዲን ሰዒድ ያስቆጠረው። ከሁለተኛዋ ግብ መቆጠር በኋላ ተመልካቹ ደስታውን የገለፀበትን መንገድ በፅሁፍ መግለፅ በጣም ከባድ ነበር። በደስታ ማዕበል እየተናጠ በሚገኘው ተመልካች ውስጥ ወደ ጨዋታው መጠናቀቂያ ላይ የግብጠባቂው የጀማል ጣሰው መጎዳት እና የአዲስ ህንፃ እርሱን ተክቶ መግባት የነፍስ ግቢ ውጭ የምጥ ሰዓት ሆነ። የመሐል ዳኛው የጨዋታውን መጠናቀቅ በፊሽካ ድምፃቸው ሲያበስሩ፣ በድምር ውጤት 5-5 በሆኖ ከሜዳ ውጭ ብዙ ባስቀጠረ ሕግ ኢትዮጵያ ከ31 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ወደመሰረተችው አፍሪካ ዋንጫ ለ10ኛ ጊዜ በመሳተፍ ዳግም መመለስ ቻለች።ይህች ዕለት የኢትዮጵያ እግርኳስን በብዙ መንገድ አነቃቅታለች፣ ከሜዳ የራቀውን ተመልካች ወደ ሜዳ መልሳለች፣ ለኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች በውጪ ሀገራት የመጫወት ዕድል እንዲያገኙ አስችላለች፣ እግርኳሱም ትኩረት እንዲያገኝ አግዛለች። ይህችን አይረሴ ገጠመኝን በትውስታ አምዳችን የወቅቱ የቡድኑ አንበል የነበረው ደጉ ደበበ ወደኃላ ተመልሶ ጊዜውን እንዲህ ያስታውሰዋል።በታሪክ አጋጣሚ ከረጅም ዓመት በፊት ካልሆነ በቀር ለአፍሪካ ዋንጫ ጫፍ የድሰ ቡድን በእኔ ዕድሜ አላየሁም። ይሄን ጫፍ የደረስንበትን ጉዞ አሳክተን ታሪክ ለመስራት ሁላችንም የቡድን አባላት ከፍተኛ ተነሳሽነት ይዘን ነው ሱዳን የሄድነው። ጥሩ ተንቀሳቅሰን ጎሎችንም አስቆጥረን ጨዋታውን ተቆጣጥረን ነበር። ሆኖም ሁሌም በብሔራዊ ቡድንም፣ በክለቦቻቸውም በሚታወቁበት መንገድ ዳኞች ይይዛሉ። ለዚህም የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ ይከፍላሉ። አይደለም ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሜዳቸው ወሳኝ ጨዋታ ለማድረግ እንዲሁም በሴራ ይታወቃሉ። ያው የፈራነው ደርሶ በሚያሳዝን ሁኔታ በመጨረሻ ደቂቃ ሁለት ፍፁም ቅጣት ምት አግኝተው 5-3 አሸንፈውን ተመለስን።በሆነው ነገር ወደኃላ ማብሰልሰል አልፈለግንም። አስራ አንድ ለአስራ አንድ ተጫውተን ከሆነ ከሜዳ ውጭ በተፈፀሙ ሥራዎች እንዳሸነፉን እናውቃለን። ስለዚህ በሜዳችን ይህን ውጤት ቀልብሰን አንድ ታሪክ መስራት እንደምንችል አምነን የመሥራት አቅሙ፣ ቁጭቱ፣ ከፍተኛ ፍላጎቱ እና የህዝቡን ጉጉት ይዘን ለጨዋታው ስንዘጋጅ ቆይተናል።የጨዋታው ዕለት ወደ ጠዋት አካባቢ ቅድመ ጨዋታ ስብሰባ እያደረግን ሁላችንም ላይ ጭንቀት ይታያል። ስታዲየም ሞልቶ የተመለሱ ደጋፊዎች በሆቴሉ ዙርያ ተሰብስበው እየጨፈሩ እያበረታቱን ነው። ይህ የበለጠ ኃላፊነቱ እየጨመረ ጭንቀት ውስጥ ከቶናል። አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ስለ ጨዋታ አቀራረብ ሊያስረዳን እጁን ጥቁር ሰሌዳ ላይ አድርጎ መፃፍ ሊጀምር ሲል እጁ ይንቀጠቀጥና መፃፍ ያቅተዋል። በዚህ ሰዓት መቼም የማልረሳውን አንድ ንግግር ተናገረ “ልጆች ቢቸግራችሁ እንኳን አሰልጣኝ እንዳትሆኑ” አለ። ይህን ያለው ከራሱ ስሜት አንፃር አይደለም፤ የህዝቡን ስሜት አይቶ ነው።በጣም የሚገርም ነበር። ከሸበሌ እስከ አዲስ አበባ ስታዲየም በምናደርገው ጉዞ ውስጥ መንገዱ በደጋፊዎች ተጨናንቆ “አታሳፍሩንም” እያለ ይጨፍራል። በብዙ ጥረት ነው ስታዲየም የደረስነው። ይህን ስታይ የሚሰማህ ስሜት እና ጭንቀት በምንም ቃላት የሚገለፅ አይደለም። ከመላው ኢትዮጵያ ከአራቱም ማዕዘን ነው ሰዉ የወጣው፤ ከፍተኛ ጉጉት አለ። ስታዲየም ደርሰን መልበሻ ክፍል ስንገባ ምን እንደሆነ አናውቅም ሁሉም ጥግ ይዞ ያለቅሳል። እኔ አሁን ለምን እንዳለቀስን ብትጠይቀኝ አላቀውም። የሆነ ሆድ የሚበላህ ነገር አለ አይደል። በቃ እናለቅስ ነበር። ፈጣሪ ረድቶን ይህን ህዝብ የምናስደስትበትን መንገድ እያሰብን ወደ ሜዳ ገባን።ከነበረን ከፍተኛ ጉጉት የተነሳ በመጀመርያው አጋማሽ ጎል ለማስቆጠር ተቸግረናል። ሰዓቱ እየገፋ በሄደ ቁጥር ደግሞ የበለጠ ጭንቀቱ ከፍ እያለ መጣ፤ ተመልካቹም በዝምታ ተውጧል። እረፍት ደርሶ መልበሻ ክፍል እንደገባን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው እየተቆጣ በከፍተኛ ድምፅ እየጮኸ “ጨዋታው አልቆ ከምንቆጭ ከሜዳ ውጭ ያለውን ነገር ትተን ወደ ራሳችን ወደ ቀልባችን ተመልሰን ታሪክ መስራት ካለብን አሁን ነው።” እያለ ነገረን። እኛም የምንችለውን እንድርገን ህዝቡን ለማስደሰት ተነጋግረን ወደ ሜዳ ተመለስን።ኡ…! ወዴት እንደሄድኩ አላውቀውም፤ በጣም ከባድ ጥያቄ ነው። ምንም የማቀው ነገር የለም። የማስታውሰው አንድ የውስጥ ስሜቴን ልንገርህ። በቃ የሳላዲን ጎል በተቆጠረበት ቅፅበት ጨዋታው ቢጠናቀቅ ብዬ አስቤ ነበር። (…እየሳቀ)እንዴ…! የሳላ ጎል ከተቆጠረ በኃላ ጨዋታው ሊጠናቀቅ አስራ ምናምን ደቂቃ የቀረው ሳይሆን ሁለት ሰዓት የቀረው ነበር የመሰለኝ። እንዴ በጣም ከባድ እኮ ነው። ብርድ እንደመታው ሰው እግራችን ይንቀጠቀጥ ነበር። ፍርሀቱ ጭንቀቱ ቀላል አልነበረም። አሁን ሁሉ ነገር አልፎ ስናወራው ቀላል ይመስላል። እንኳን እኛ በመላው ዓለም ይህን ጨዋታ የሚከታተለው ህዝብ እንዴት ይቁነጠነጥ እንደነበረ መገመት ከባድ አይደለም። አስበው ሸክሙን የተሸከምነው እኛ ደግሞ ምን እንደምንሆን። ፈጣሪ ፈቅዶልን ሁሉ ነገር በድል አለቀ።ኡ ፍ ፍ…! (እየሳቀ) እኔ ወንድ ነኝ፤ የእናቶቻችንን ምጥ አላውቅም። ባለቤቴ ግን ምጥ ምን እንደሆነ ስትነግረኝ አውቃለው። በቃ በሆዳችን የነበረውን ነገር አምጦ የመውለድ ያህል ነው የነበረው ስሜት። ይህ የግል ስሜት፣ ፍላጎት ቢሆን ችግር የለውም ቀላል ነው። ምክንያቱም ብቻህን ነው ጭንቀቱን የምትወጣው፤ ይህ ግን ሀገር ነው። ህዝቡ እንዴት እያበደ እንዳለ ይታወቃል። ያ ሁሉ ኃላፊነት እና ከባዱ ፈተና አልፎ ይህ በመሆኑ ደሰታዬን ለመግለፅ ከባድ ነው። በእግርኳስ ህይወቴ ሁሌም ደስተኛ ነኝ። ይህ ቀን ግን እጅግ በጣም የተለየ ቀን ነው።", "passage_id": "30c8377483083a14cd81a67c1b5c50d5" }, { "passage": "በአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ወደ ሩብ ፍፃሜ ለማለፍ የሚደረገው ውድድር ዛሬና ነገ ይቀጥልና ከየምድቡ ያለፉት 8ቱ ቡድኖች ይለያሉ።ከወዲሁ ማለፋቸውን አረጋግጠው የተቀመጡት አራቱ ቡድኖች ካሜሩን፣ ቡርኪና ፋሦ፣ ሴኔጋልና ቱኒዝያ ናቸው።ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። ", "passage_id": "1f2925a77c125e9c43ce71fba4392cf1" } ]
364ed43b49c59d59ba329703d145c101
3fbd58382c3ed2d1fbcfea3a6c1bf46b
”በወረቀት የሰው በደም የእኛ ናቸው»
በረሃማነት በእጅጉ ከሰፈነባቸው የአረብ ሃገራት ነዳጅ እንጂ አትሌት ይፈልቃል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ በሪዮ ኦሊምፒክ የታየው ግን ተቃራኒ ነበር፡፡ በአማዞን ጥላ ስር በተካሄደው የቁንጮ አትሌቶች ፍልሚያ ባህሬን የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ስታስመዘግብ የተለየ ትኩረት የሰጣት አልነበረም፡፡ ሁለተኛውን ስትደግም ግን ዓለም አይኑን ሊጥልባት ተገደደ። ባህሬን ሰንደቅአላማዋን በዓለም ሕዝብ ፊት ከፍ አድርገው ያውለበለቡላት አትሌቶች የኋላ ታሪክ ሲጠናም አምጣ ወልዳ አየሯን ተንፍሰው ያደጉ ሳይሆኑ ከሚስኪኗ አህጉር አፍሪካ ማህፀን የወጡ ኬንያዊያን መሆናቸው ተገለጠ፡፡ ይህ አይነቱ አጋጣሚ ለባህሬን ብቻም ሳይሆን ለአሜሪካ እና ለቱርክ በጥቅሉ ከ30 በላይ የሚሆኑ ኬንያዊያን በወረቀት ላገኙት ዜግነት እንደሚሮጡ መታወቁ አነጋጋሪ ነበር፡፡ ይህ በአትሌቲክስ ብቻ ሲሆን በሌሎች የኦሊምፒክ ስፖርቶችም የደም ሳይሆን የወረቀት ዜግነት ላገኙባቸው በርካታ አገራት የተለያዩ አትሌቶች አንፀባርቀዋል፡፡ኑሮን ለማሸነፍ በየተኛውም ዘርፍ ጠንክሮ መሮጥ የግድ በሆነባት ዓለም በቀጥተኛው መንገድ መጓዝ አሊያም አቋራጮችን መጠቀም የግድ እየሆነ ይመስላል፡፡ ከእነዚህ አቋራጮች መካከል አንዱ ደግሞ የተሻለና ምቹ ሁኔታ ወዳላቸው ባለፀጋ ሃገራት መጠጋት ነው፡፡ ይህ ሁኔታ በዚህ ወቅት የተለመደ ሲሆን፤ በርካታ አትሌቶች በዚህ መልክ የፈለጉትን አሳክተዋል፡፡ በአትሌቲክስ የተሻለ ብቃት ያላቸው የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ደግሞ አትሌቶቻቸውን ለሌሎችም በማጋራት ቀዳሚዎቹ ናቸው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ የኬንያ፣ የናይጅሪያ፣ ሞሮኮ፣ የኢትዮጵያ አትሌቶችም ከትውልድ ሃገራቸው ቀጥሎ አሜሪካ፣ የአውሮፓ እና አረብ ሃገራት ዋነኛ መዳረሻቸው ነው፡፡ ሃገራቱም ያላቸውን የኢኮኖሚ ጡንቻ በመጠቀም አትሌቶችን ከማስኮብለል ወደኋላ አይሉም፡፡ ለአብነት ያህል በሪዮ ኦሊምፒክ ኳታር ካሰለፈቻቸው 39 አትሌቶቻ 23 የሚሆኑት ትውልዳቸዉ በሌሎች ሃገራት ነው፡፡ ሃገሪቷ እአአ በ2000 በአንድ ውድድር ላይ ለማሳተፍ ስምንት ቡልጋሪያዊያንን በአንድ ሚሊዮን ዶላር ማስማማቷን ፋይናንሻል ታይምስ ያስታውሳል፡፡ እንግሊዝም ብትሆን እአአ 2012 ባስተናገደችው ኦሊምፒክ ካሳተፈቻቸው 542 ስፖርተኞች መካከል 60 የሚሆኑት እትብታቸው በሃገሪቷ ያልተቀበረና በወረቀት ዜግነት ያገኙ ነበሩ፡፡ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር እአአ ከ2000-2017 በየሃገራቱ ባደረገው ጥናት መሰረት የኀያሏ ሃገር አሜሪካ ፍላጎት በማሻቀቡ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፡፡ ባህሬን፣ ኳታር እና እንግሊዝ ደግሞ ተከታዮቹ ሃገራት ናቸው፡፡ በዶሃው ቻምፒዮና በ1500ና 10ሺ ሜትር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት ወርቅ ያጠለቀችው የኑዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰንን ጨምሮ የዓለም ቻምፒዮኗ አበባ አረጋዊ፣ ኤልቫን አቢይ ለገሰና ሌሎችም በርካታ ስመ ጥር አትሌቶች ‹‹በወረቀት የሰው በደም የዕኛው ናቸው››፡፡ ከሰላሳ በላይ የሚሆኑ አትሌቶቿም በወረቀት ላገኙት ዜግነት ከአገራቸው ወጥተው እየሮጡ ይገኛሉ፡፡ ባህሬን፣ ቱርክ፣ ኳታር፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ሆላንድ፣ እንግሊዝ፣ ፖላንድ፣ ቤልጂየም፣ ስፔን፣ ስዊድን፣ ጀርመን እና አሜሪካ ደግሞ ዜግነት የሰጧቸው ሃገራት ናቸው። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነም በዚህ ወቅት በመቶዎች የሚቆጠሩ አትሌቶች የተለያዩ ሃገራትን መለያ ለብሰው ይሮጣሉ፡፡ አንዳንዶች ለዚህ በምክንያትነት ድህነትንና በፌዴሬሽን በኩል ያለ ብልሹ አሰራርን ምክኒያት አድርገው ያነሳሉ፡፡ ቱርክን በተለያዩ ኦሊምፒኮች የወከለው ትውልደ ኬንያዊው አትሌት አክዳክ አሌክስ ኪፕኪሩይ፤ ‹‹ወላጆችን ጨምሮ የማስተዳድራቸው አራት እህት እና ወንድሞች ነበሩኝ፤ ኑሮን ለማሸነፍ ስሮጥም አንድ አሰልጣኝ ፈቃደኛ መሆኔን ጠየቀኝ›› ሲል ሁኔታውን ፌር ፕላኔት ለተባለ ድረ ገጽ አስታውሷል፡፡ አሁን ቤተሰቦቹ በሚፈልጉት ሁሉ እየረዳቸው ሲሆን፤ የታናናሾቹን የትምህርት ወጪም መሸፈን ችሏል፡፡ በርካቶች በእንዲህ አይነቱ ጉዳይ እንደይስማሙ ይታወቃል፤ ምክንያታቸው ደግሞ ገንዘብ ከሃገር አይበልጥም የሚል ነው፤ ኪፕኪሩይ ግን ከድህነት አላቆታልና በዚህ አይስማማም በድርጊቱም እንደምይጸጸት ነው የሚገልጸው፡፡ ኬንያ ሳለች ማሪያም ጅፕቶ ትባል የነበረችው ሌላኛዋ ባህሬን ዜጋዋ ያደረገቻት አትሌትም የኪፕኪሩይን አስተሳሰብ ትጋራለች፡፡ ስሟን አሊያ ባስማ በሚል የቀየረችው አትሌቷ ኬንያ ውስጥ በርካታ ወጣት አትሌቶች ቢኖሩም ለዓለም አቀፍ ውድድሮች የመታጨት እድላቸው አነስተኛ መሆኑን ትጠቁማለች፡፡ ለልሎች ሃገራች የመሮጥ እድል ቢመቻችላቸው ግን በኦሊምፒክ እና ዓለም ቻምፒዮናዎች ላይ ለመሳተፍ እንደማይቸገሩ ልምዷን ታካፍላለች፡፡ በርካታ አፍሪካዊያን አትሌቶች የመነሻ ምክንያት ኑሮን ማሸነፍ ይሁን እንጂ የተቀሩት ደግሞ በልጅነታቸው በማደጎ ወደ ሌላ ሃገራት በመሄድ እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመሰደድ ነው ሁለተኛ ሃገርን የሚወክሉት፡፡ በተለይ የሰሜን አፍሪካ ሃገራት ወደ አውሮፓ በሚያደርጉት ስደት ምክንያት እግር ኳስ እና አትሌቲክስን ጨምሮ በሌሎች ስፖርቶች ተሳታፊ የሆኑ አትሌቶች ከትውልድ ሃገራቸው ይልቅ ላደጉበት ሃገር ለመወዳደር ይገደዳሉ፡፡ የተቀሩት ደግሞ በሃገራቸው ምቹ ሁኔታ ባለማግኘትና በመገፋታቸው በቀላሉ ዜግነት ወደ ሚሰጧቸው ሃገራት ያማትራሉ። በስፖርት አመራሮችና አሰልጣኞች ያለው የቀናነት ጉድለት፣ ለብሄራዊ ቡድን በሚደረገው ምርጫ የሚቀመጠው የማያስማማ መስፈርት፣ ለስፖሩቱ እና ለአትሌቶቹ የሚሰጠው ትኩረት አነስተኛ መሆን፣ አትሌቶቹ የሚከፈላቸው ደመወዝ አነስተኛ መሆን፣ በልምምድ እና በማገገሚያ ወቅት በቂ ቁሳቁስ እንዳስፈላጊነቱ ባለማግኘት እና ሌሎች ምክንያቶችም አትሌቶች ከትውልድ ቀያቸው ይልቅ የሌሎች ሃገራትን ክብር እንዲገነቡ ሆነዋል፡፡ ወደ ባለጸጎቹ የመካከለኛው ምስራቅ አረብ ሃገራት መጓዝ ለአትሌቶቹ የተሻለ ነገር እንደሚያስገኝ ይታሰብ እንጂ፤ በተቃራኒው የስፖርት ባርነትን እንደሚያተርፍም ዘ ጋርዲያን የተሰኘው ድረገጽ በአንድ ዘገባው አስነብቧል፡፡ ኢትዮጵያዊቷ ሊሊ አብዱላይቫ ያሰቡት ካልተሳካላቸው አትሌቶች መካከል ትተቀሳለች። አትሌቷ ለቱርክ ለመሮጥ የተስማማችው በ300ዶላር ወርሃዊ ክፍያ እንዲሁም ስታሸንፍ ተጨማሪ 1ሺ ዶላር ሊከፈላት እንዲሁም ቤትና መኪና ሊሰጣት ነበር። ይሁን እንጂ ቃል የተገባላት አልተፈጸመላትም፣ የሽልማት ገንዘቧንም ማግኘት አልቻለችም፡፡ ሌላኛው ኬንያዊ ልዮናርድ ሙቹሩም የዚህ ታሪክ ገፈት ቀማሽ ነው፡፡ አትሌቱ ጉዳት ባጋጠመው ወቅትም የባህሬን አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ደመወዙን ሊሰጠው ፈቃደኛ እንዳልነበረም ገልጣል፡፡በርካቶች ጉዳዩን ከህገወጥ ሰዎች ዝውውር ለይተውም አያዩትም፤ ዓለም አቀፍ ውድድሮችንም አደጋ ላይ ይጥላል በሚል ይገልጹጻል፡፡ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበርም በተመሳሳይ በዚህ ጉዳይ አይስማማም፤ ማህበሩ ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ በአትሌቲክስ እና እግር ኳስ ስፖርቶች ዜግነት እንዳይቀይሩ የሚከለክል ጠንካራ ህግ ባለመኖሩ ይህ ዓይነቱ ዝውውር እያደገ መምጣቱ አሳሳቢ መሆኑን በአንድ ወቅት ተናግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ አትሌቶችም ኦሊምፒክን መሰል ትልልቅ ውድድሮች ሲቃረቡ ወደ ዜግነት መለወጥ እንቅስቃሴ ይገባሉ፡፡ በመሆኑም በቅርቡ አዲስ ደንብ የሚወጣ መሆኑን ጠቁመው ነበር እስካሁን ምንም የተባለ ነገር ባይኖርም፡፡ በእርግጥ ከሁለት ወይም ከሦስት ዓመታት በፊት የወጣ አንድ ህግ አለ፡፡ ይህ ህግ አንድ አትሌት ዜግነቱን ቀይሮ ከመሮጡ በፊት ለትውልድ አገሩ ለሁለት ዓመታት መሮጥ እንዳለበት የሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ግን አትሌቶችን ከስደት የሚታደግ አልሆነም፡፡ አዲስ ዘመን ጥቅም30/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22258
[ { "passage": "ወራሪው የፋሺስት ጦር ሀገራችንን በቅኝ ለመግዛት በዘመተበት ወቅት ጀግኖች ኢትዮያውያን አይበገሬነታቸውን በተግባር አሳይተውታል።አዲስ አበባን ማዕከል አድርጎ በቆየበት ጊዜና በየካቲት 12 ቀን 1929 ዓም የሆነው ግን ከሁሉም ይለያል። በዚህች ቀን የግራዚያኒ ጦር ለድሆች ምጽዋት እሰጣለሁ ሲል መኳንንቶችን ሰበሰበ። ይህን አጋጣሚ ለመጠቀም የፈለጉት ወጣቶቹ ሞገስ አስገዶም፣ አብርሀም ደቦጭና ስምኦን አደፍርስም በግራዚያኒ ላይ የእጅ ቦንብ ወርውረው ክፉኛ አቆሰሉት። ይህኔ የድርጊታቸውን አጸፋ ለመመለስ የፈለገው የኢጣሊያ ጦር በከተማው ነዋሪዎች ላይ የጭካኔ በትሩን አሳረፈ። ለሦስት ቀናት በቀጠለው እልቂት ከሳላሳ ሺህ በላይ አረጋውያን፣ ነፍሰጡር እናቶች፣ ጡት ያልጣሉ ህጻናት፣ ወጣቶች፣ አካልጉዳተኞችና ሌሎችንም እያሳደደ በአካፋና በዶማ ጨፈጨፋቸው። የተቀሩትንም በጥይት ደብድቦ በመግደል በቤንዚን አርከፍክፎ አቃጠላቸው። ከተማዋ በደም ተጥለቀለቀች። የንጹሀን ህይወትም በከንቱ አለፈ። እነሆ! ይህ ታሪክ ከተፈጸመ ሰማንያ ሁለት ዓመታት ተቆጠሩ።ይህን አይረሴ ታሪክ በቀላሉ የማይዘነጉት ኢትዮጵያን ግን ዛሬም ቀኑንና ሰማዕታቱን እንዲህ አስበው ውለዋል። ", "passage_id": "8d01a9e78dc68cf518223f6aee12eb61" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 17/2012 ዓ.ም (አብመድ) ‘‘ያልጠረጠረ ተመነጠረ’’ እንዲሉ ጠርጣራ መሆን መልካም ነው። ታዛዥ መሆንና ምክርን መስማት ደግሞ ታላቅነት ነው።አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን እንደየአመለካከታቸው ልህቀት የሚያመልኩት ወይም የሚፈሩት አንድ ኃይል አላቸው፤ ምሥጋና ሰጥተውም በረከት ይቀበላሉ። እንዳይጠፉ ለምነው መከራን ይሻገራሉ። ‘‘ዓለም በሸጠችው ክፉ ሥራ ልክ ክፉ ነገርን መቀበል ከጀመረች ወራት ተቆጥረዋል፤ ኃያላኑ አንገት ደፍተዋል። ‘ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ’ ያሉት ሁሉ ሞተዋል። ያልተገዙት ከዋክብት፣ ፈጣሪያቸው፤ ያልተመሰገነው ፀሐይ እና ጨረቃ ተናፍቀዋል። ያለገንዘብ የተመጠጠ ንፁህ አየር፣ ያለ ተቆጭ የለፈለፈ አፍና ከንፈር ዛሬ ላይ ዝግ ነው። በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዓለም ሕዝቦች በቤት ጣራ ሥር ተደብቀው የሞትን መልአክ እየጠበቁ ነው። ዕድለኞች ከሞት ጥላ ስር አዳኝ መልአክ እየደረሰ ይመልሳቸው ጀምሯል። ብዙዎች ግን በማዕበሉ ተመትተው፣ ከልጅ ፍቅር ተለይተው የማይጠግቧትን ዓለም ተሰናብተው እስከወዲያኛው አልፈዋል’’ እያሉ ሰዎች ወደ መልካም ምግባርና ሃይማኖት ፊታቸውን እንዲያዞሩ የሚመክሩም በዝተዋል።በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ከሥራ ዓለም የተሰናበቱትንና አሳዳጊ አልባ የቀሩት ሰዎችማ ቤታቸው ይቁጠራቸው። መቃብሮች በዙ፣ እልፍ አዕላፍ አስሬኖች በየቀኑ በተከፈተው መቃብር ሥር ለመግባት ተጓዙ። የሞትን ከባድነት የቀብር አፈር ያላለበሰ፣ በወዳጅ ሞት እንባ ያላፈሰሰ፣ ነጭ መብሩቅ አውልቆ ጥቁር ያለበሰ ላያውቀው ይችላል። ነገር ግን ‘‘ብልህ ከጎረቤቱ ይማራል’’ እንዲሉ የሌሎች ሞት ለዘመዶቻቸው ሐዘን እና ፀፀት ከሩቅ ሆኖ ለሚመለከተው ደግሞ ትምህርት ሆኖ ያልፋል።ዓለምን እንደ ውጋት ወገቧን ሰቅዞ አላላውሳት ያለው ይህ በሽታ በሩቅ ምሥራቋ አገር ለዚያውም በሁለተኛዋ ኃያል አገር ከተከሰተ ቀን ጀምሮ የሰውን ልጅ ባሕሪ ለሁለት ከፍሎ ቁልጭ አድርጎ ያሳዬን ጀምሯል። ይበሉት ጉርስ ይለብሱት ልብስ የሌላቸው ምስኪናን ሳይጠግቡና ሳይለብሱ እኔ አልደሰተም የሚል አዛኝ፣ የሟቾች ቁጥር በጨመረ ቁጠር ከሬሳ ሳጥን ላይ አትርፎ ለመክበር የሚታትር የሞት ወረፋውን በውሉ ያላወቀ ስግብግብ፣ ‘‘ልጆቼና ቤቴ በደስታ ቀን እንገናኝ’’ ብለው ሕይወታቸውን ለታማሚዎች የሰጡ የጤና ባለሙያዎች፣ የቀን ሥራ ሠርቶ ባጠራቀማት ብር ነገ እንቅስቃሴ ከተዘጋ ብሎ ብትን በርበሬ ከሚገዛ ምስኪን ሕዝብ ላይ አትርፈው ለመክበር እንቅልፍ ያጡ ሞኛሞኝ ነጋዴዎች፣ በሽታው የኢትዮጵያን ምድር ከነካበት ቀን ጀምሮ ‘‘ብርሃን ለምኔ፣ ሰው እንዳላይ፣ ዘመድ መጠየቅ ይቅርብኝ፣ በሬን አታንኳኩ’’ የሚሉ ፈሪ ተጠንቃቂዎች እና ‘‘በሽታው ኢትዮጵያውያንን አይገድልም፤ እኔንም አይደፍረኝም፤ ገደለ ከተባለም በዕድሜያቸው የገፋውን እንጂ ከወጣት ጋር ጨዋታ የለውም’’ የሚሉ ሞኝ ራሱን ገዳይም በምድሪቱ ሞልቷቶ ታዝበናል።ቀን ካላወቁበት ያስተዛዝባል፤ ካወቁበት ደግሞ ያስተዛዝናል፤ ያስተዛዝላልም። ‘‘ያገኜም ያጣና ያጣም ያገኝና ያስተዛዝበናል ይኼ ቀን ያልፍና’’ አይደል ያለው አዝማሪውስ? ምን ይኼ ብቻ ‘‘የሚሞት ሽማግሌ አይርገምህ፤ የሚያድግ ልጅ አይጥላህ፤ የሚያልፍ ዝናብም አይምታህ’’ ይላሉ ቀደምቶቻችን ሲመክሩ። ታግሶ እና አስታውሎ ከሽማግሌው እርግማንም፣ ከሚያድገው ልጅ መጠላትም ከሚያልፈው ዝናብ መመታትም መዳን ሲቻል ለምን በማይሆን ቀን የማይሆን ሥራ ሠርቶ ስምን እና ሕይወትን ማበላሸት መረጥን? ነገሩን ሁሉ በዘመን መነፀር ማዬት ከትዝብትም ከሞትም ያድናል። የጠረጠረ ይፈነጠራል፤ ያልጠረጠረ ደግሞ ይመነጠራል።", "passage_id": "93df3d69802f9c6c7dc6f994df602c35" }, { "passage": " ባሕር ዳር፡ ኅዳር 08/2013 ዓ.ም (አብመድ)ሲሞግቱን እንረታቸዋለን፣ ሲገጥሙን እንመታቸዋለን፣ ሲገምቱን ከአቅም በላይ እንሆንባቸዋለን ኢትዮጵያዊያን ለጠላት አንችመችም፡፡አፈጣጠራችን ለጣለት መብረቅ ለወዳጅ መረቅ ነው፡፡ ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዉያንና የኢትዮጵያን የማይፈልግ የለም፡፡ ፍላጎቱ ለክፋት ወይም ለበጎነት ሊሆን ይችላል፡፡ ብዙዎቹ ግን የሚፈልጓት ታሪኳን ሊዘርፉ የእነርሱ ሊያደርጉ ነው፡፡ይህ ሲሆንላቸው አልታዬም፣ አይታይምም፡፡ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዉያንን ማሸነፍ የሚቻለው ይሁን ይደረግላችሁ ብሎ በመፍቀድ ብቻ ነው፡፡ ዓለም ኢትዮጵያን የሚያሸንፍበትን አማራጭ ሁሉ ሞክሯል አንዱም አልተሳካም፡፡ ቀሪ ያልሞከሯቸው ነገሮች ካሉም አይሳካም፡፡ ስለማይችሉን አይወዱንም፤ ስለሚፈልጉን አይተውንም፤ ስለማይሆንላቸው አያሸንፉንም፤ አፈጣጠሯና አኗኗሯ ሚስጥር ነው፡፡ ሚስጥሩን የሚፈታው ደግሞ የሚጥሩ ባለቤት ብቻ ነው፡፡ ሌላው ዘበት ነው፡፡በኢትዮጵያ ላይ የተኮሱ ተመለሱ፣ ተደመሰሱ፣ ያሴሩ ተቀበሩ፣ ታሪክ የሚያሳዬው ይሄን ነው፡፡ ለጠላት መጋኛ የሆነ አርበኛ መውለድ አዲሷ አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ወታደር የማይሰበር አጥር፣ የማይመለስ ግንባር፣ የማይፈታ ሚስጥር፣ ዝቅ የማይል ክብር ያለው ለአሸናፊነት ብቻ የተፈጠረ ነው፡፡ ዘምቶ ተሸንፎበት የመጣ የጦር ግንባር የለም፡፡በሁሉም አሸንፎ ሁሉንም አክሽፎ ነው የሚመጣው፡፡ ይህ አሸናፊነትን ከዘር የወረሰው ሠራዊት አሁንም ለሌላ አሸናፊነት እየተጓዘ ነው፡፡ የውስጡን አረም ነቅሎ የውጩን አረም ከድንበር ማዶ ለማስቀረት፡፡ስለወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይና ስለ ኢትዮጵያ ሠራዊት ጀብዱነት ከአብመድ ጋር ቆይታ ያደረጉት የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሕበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን የኢትዮጵያ አርበኞች በጀግንነት ለሀገራቸው መሥዋት ሲሆኑ የኖሩ ናቸው፤ አሁን ያለው ሠራዊት የእነዚያ ጀግኖች ልጅ ነው ይሉታል፡፡ የእነዚያ ልጆች የአሁኖቹ ሠራዊቶች በስነመግብር፣ ሀገርን በመጠበቅ፣ ሕግ በማስከበርና ሀገር ባለማስደፈር ወኔ የተላበሱ ናቸው ይሏቸዋል፡፡በጀግናው ሠራዊት ላይ የደረሰው ጥቃት እንዳበሳጫቸው የተናገሩት ልጅ ዳንኤል ከሰሞኑ ጥቃት አስቀድሞ የቀድሞ የኢትዮጵያን ሠራዊትን የደርግ ሠራዊት አባላት እያሉ ለሀገራቸው የከፈሉትን መስዋዕት ከንቱ ሲያስቀሩ ነው ስህተቱ የተጀመረው ነው የሚሉት፡፡የቀድሞው የኢትዮጵያ ሠራዊት በሶማሊያና በሌሎች ግንባሮች የፈፀመውን ገድል ከንቱ አስቀርተውበታል፤ በዚህ ሥራው ጀግንነቱ አልተነገረለትም፣ ይህ ደግሞ የሠራዊቱን ጀብዱ አለመዘከር ብቻ ሳይሆን ወዳጅ ዘመዶቹንም አንገት አስደፍቷል ብለዋል፡፡ በደረግ ሠራዊት ላይ የፈፀሙት ግፍ ባለመነገሩና ግፈኞቹ ለህግ ባለመቅረባቸው ዛሬ ላይ በሠራዊቱ ያደረጉት ነገር አዲስ ነገር ሆኖ መቅረብ የለብም ነው ያሉት፡፡ በደል መሥራት የመጡበት ነውና፡፡የመከላከያ ሠራዊት የአንድ ሀገር ደም ስር ነው፤ ደም ሥር ውስጥ ደም ኬሌለ ሕይወት የለም፤ ሠራዊቱ በዱር በገደል የሚንከራተቱት ለሀገር ለወገን ነው እንጂ ለማንም አይደለምም ብለዋል፡፡ ትህነግ በሠራዊቱ ላይ የፈፀመው በደል ከኢትዮጵያዊነት ባሕል ያፈነገጠ ክህደት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ሠራዊቱ ዘብ የሆኑት ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያዊያን እንጂ ለማንም አይደለም ያሉት ልጅ ዳንኤል የሚገባቸው ክብር ሊሰጣቸው ይገባል ነው ያሉት፡፡የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ተነክቶ ነው የተነሳው፣ ሳይነኩት አልነካቸውም አሁን ሀገርን የማዳን ሥራ እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ሕዝቡንና ጦሩን ያስቆጣው አታለው መውጋታቸው መሆኑንም በመግለፅ፡፡ የትግራይ ሕዝብ ከማንም የኢትዮጵያ ሕዝብ በላይ ጥቃት የደረሰበት ነው ያሉት ልጅ ዳንኤል ኢትዮጵያዊነቱንም ያስመሰከረ ነውም ብለዋል፡፡ትህነግ ያደረገው እኩይ ተግባር ጀልባውን በማነቃነቅና በየቦታው እሳት በማስነሳት የማዕከላዊ መንግሥቱን አቅም በማሳነስ ስልጣን ለመያዝ ነበር፤ ነገር ግን ሕዝብ ሳይፈቅድ ስልጣን መያዝ አይቻለም ነው ያሉት፡፡ ማንም ሰው በሀገሩ ጉዳይ መፍራትና ማፈግፈግ እንደማይገባውም አመላክተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሠራዊት ሕዝብን በማቀፍ ህገወጦችን ወደሕግ ለማቅረብ በሚያደርገው ተጋድሎ ሊደገፍ ይባልም ብለዋል፡፡ድህነትም ጌትነትም በሀገር ነው ያሉት ልጅ ዳንኤል አባቶች መስዋዕት የሆኑት ለሀገርና ለወገን ነው፤ ኢትዮጵያ የምትቀናባት ሀገር ስለሆነች በየትኛውም ጊዜ ጠላት አታጣም፤ የኢትዮጵያ የይቻላል መንፈስና አይደፈሬነት ጠላቶች እንዳይወዱን አድርጓል፤ ከውጭም ሆነ ከውስጥም ያሉ ጠላቶች የተቀናጁ ናቸው፤ ጠላቶቻችን ለመመከት አንድነታችን ሊጠነክር ይገባል ነው ያሉት፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመከላከያው እያሳዬው ያለውን ድጋፍ በዚሁ ከቀጠለ ጠላቱን በብቃት ይከላከላልም ብለዋል፡፡ የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሕርበርም ሠራዊቱን በሚችለው ሁሉ ለማገዝ ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡የኢትዮጵያ ሕዝብ በየትኛውም ሀገር የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆችን በመጠበቅና መንባከብ እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡", "passage_id": "234f49f6e22155a3b64854a4120ba370" }, { "passage": "ዳግም ከበደየሰሞኑ ክስተት ብዙ አሳይቶናል። የሚበጀንንና የማይለየንን ወዳጅ እንድንለይበት ምክንያት የሆነም ነበር። የመከራ ወቅት ወዳጅ ጠላትህን ትለይበታለህ እያለ ብልሃትን በሚያስተምር ማህበረሰብ ውስጥ ስለምንኖር አጋጣሚውን ለዚሁ እየተጠቀምንበት ነው። ምንም እንኳን በክፉ ጊዜ ችግርህ ላይ የምታተኩር ቢሆንም ቅሉ ነገሩ በረድ እያለ በመጣ ቁጥርና ማስተዋል አድማሱን ሲያሰፋ በዙሪያህ የሚሆነውን ሁሉ መታዘብ ስለማይቀር እኛም እየሆነብን ያለውን ሁሉ መመዝገብ ጀምረናል።ጠላት ከሩቅ አይመጣም እንዲሉ ብሂሉ ተግባር ላይ ውሎ ጉያችን ውስጥ ያሉ ወንድሞቻችን ጦር ሰብቀውብን እንደ እየሱስ ክርስቶስ ኢትዮጵያን ጎኗን በጦር ወግተዋታል። ይህ አልበቃ ብሏቸው ሰላም ፈላጊነታችን ላይ ተሳልቀዋል። ወንድም ወንድሙን ሲያማው እንደሚሰቀጥጠው ሁሉ በዙሪያችን እየተሽከረከሩ ተጨማሪ ጠላት ሊሸምቱልን ላይ ታች ደፋ ቀና ሲሉ አስተውለን እንዳላየ አልፈናል። ታሪክ እንዲህ ይለናል። ኢትዮጵያ ከጉያዋ በሚወጡ ባንዳዎች ለዘመናት ጀርባዋን ስትወጋ ኖራለች። ጀግኖች አርበኞቿ ደግሞ ይህን ዓይን ያወጣ ብልግና ሲመክቱ አገራቸው ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ደጀን ሲሆኑ ኖረዋል። ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ\nበፓርላማ ተገኝተው ወንበዴዎቹ\nአገር ለማፍረስ ሲታትሩ\nድል እንደተመቱ ይፋ\nሲያደርጉ ምን ነበር\nያሉት፤ ‹‹እንግዲህ ምን\nታደርጉት እኛም ያባቶቻችን\nልጆች ነን። ጀግንነታቸውን\nበጎ አላማቸውን ወርሰናል››\nበማለት አገር ለማፍረስ\nከሰይጣን ጋር ተወዳጅተው\nበእኩይ አላማቸው ነሁልለው\nዘራፍ የሚሉትን የባንዳ\nልጆች የኢትዮጵያ መከላከያ\nሰራዊት በታላቅ ድል\nመክቶ የቀበሮ ጉድጓድ\nውስጥ እንደከተታቸው ሲናገሩ\nበታላቅ ወኔና ኢትዮጵያዊ\nመንፈስ ነበር። ከሁሉም ከሁሉም ግን ወንድሞቻችን ጦር ሰብቀው ስለወጉን ብቻ አልነበረም ቁጭትና እልህ ውስጥ የገባነው። ይልቁንም የዚህን እኩይ ቡድን አላማ ከውጭ ሆነው ፖለቲካዊ ጥቅማቸውን ለማሳካት ሲሉ መደገፋቸው ይበልጥ የሚያንገበግብ ነበር። ለዚህ ነው ክፉ ጊዜ ወዳጅና ጠላትን ለመለየት ይጠቅማል የሚለው የአገሬ ሕዝብ።ታሪክ ደግሞ እንዲህ ይለናል። ቀድሞውንስ ቢሆን የውጭ ኃይሎች ሉዓላዊነታችንን በፀጋ ለመቀበል መች ፈልገው ያውቃሉ? ለሺህ ዘመናት የተገነባ አገረ መንግሥት ያላት ኢትዮጵያ ግን በውስጥ ጉዳይ ላይ ሊፈተፍቱ የሚሹ እኩያንን ስትመክት ዳር ድንበሯን ስታስከብር ኖራለች።ከሰሞኑ ደግሞ ዓለም አቀፍ ተፅእኖ መፍጠር እንችላለን የሚሉ አካላት መንግሥትን ለመወጠር እና ቅርቃር ውስጥ ለመክተት የሚያደርጉት መንፈራገጥ እያስገረመን ነው። አንዳንዶች የኢትዮጵያውያንን አኩሪ ታሪክና ሉአላዊነት በማክበር በሕግ ማስከበርና በውስጥ ጉዳያችሁ አንገባም ብለው እጃቸውን ሲሰበስቡ፤ በተቃራኒው ግን በሰው ጉዳይ ላይ እንደ እርጎ ዝንብ በመግባት ሰፊ ታሪክ ያላቸው አካላት እጃቸውን ለመዶል ሲጋጋጡ እያስተዋልን ነው። በፌዴራል እና በትግራይ ክልል መንግሥታት መካከል ድርድር ይካሄድ የሚሉ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ድርጅቶችም ይሁኑ አገራት በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውንና እየተካሄደ ያለውን በትክክል ያልተገነዘቡ ናቸው። በርካታ አስተያየት ሰጪዎች የድርድር ጊዜው ማለፉን ገልጸዋል። ይሄ ሃሳብም በሁሉም መመዘኛ ትክክል ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርላማ ተገኝተው ላለፉት ዓመታት መንግሥት ከጁንታው ቡድን ጋር ድርድር ለማድረግ እጅግ ብዙ ጥረቶችን ማድረጉን ጠቅሰዋል፤ ቡድኑ ግን የመፍትሄ ሃሳቦችን ሲገፋና በንቀት ልቡን ሲወጥር ቆይቷል። አሁን ላይ ግን የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ለማደናገርና ጊዜ ለመግዛት ድርድር ፈላጊ አስመስሎ ራሱን አቅርቧል። የአደራድሩኝም እየዬውንም በውጭ አገራት ባሰማራቸው ግልገል ባንዳዎች እስከ ሽንፈቱ ዕለት ድረስ ሲነዛ ቆይቷል።ጁንታው ለማደናገሪያነት ወቅታዊው ችግር በፖለቲካ መፍትሔ እንዲያገኝ ደጋግሞ የጠየቀ ቢሆንም፣ የፌዴራል መንግሥት በበኩሉ ድርድር እንደማይኖርና የመጨረሻ የተባለው ሕግ የማስከበር ተግባር በቀጣይ ቀናት እንደሚከናወን በጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካኝነት ግልፅ ማድረጉ የሚታወስ ነው። ይህን እቅዱንም ሙሉ ለሙሉ በማሳካት ቃሉን ወደ ተግባር ቀይሮታል። የትግራይን ሕዝብ ከዚህ እኩይ ቡድን በመነጠል ቀበሮ ጉድጓድ ውስጥ እንዲመሽግ አድርጎታል።በዚህ ሰዓት ነው እንግዲህ አንዳንድ ምዕራባውያንን ጨምሮ የቀድሞ ዲፕሎማቶች መቅበዝበዝ የጀመሩት። ሁሌም ቢሆን በሰላም ማስከበር ስም ዳግማዊ የቀኝ ግዛት ሰንሰለት ለመዘርጋት የሚጥሩ መሆናቸው ይታወቃል። በዚህ ምክንያት ነው አገራቱ የጁንታው አከርካሪ መሰበር አልዋጥ ብሏቸው በየሚዲያው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሙሉ ለሙሉ የደገፈውን ዘመቻ ሲያብጠለጥሉ የተደመጡት። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን ለዚህ ቁርጥ ያለ መልስ የሰጡ ይመስለኛል።በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ምስረታ ታሪክ ኢትዮጵያ በነጮች ዓለምን እንደፈረስ የመጋለብ ቅጥ ያጣ ህልምና የቀኝ ግዛት መቧቸር ውስጥ ያልተካተተች ሉአላዊ አገር መሆኗን ታሪክን በማጣቀስ አስረድተዋል። ይህቺ የሥልጣኔ ጀማሪ የሰው ልጆች ልክ መገኛ ከአፍሪካ አገራት በብቸኝነት ቅኝ ካለመገዛቷም ባሻገር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መስራች መሆኗንም ጠቅሰዋል።ታዲያ ይህን ሁሉ ምሳሌ ሲያጣቅሱ እንዲሁ ለይስሙላ እንዳልነበር ገልፀዋል። ይልቁንም ምዕራባውያኑም ሆኑ አንዳንድ የዓለም አቀፍ ተቋማት የትህነግን እስትንፋስ ለማስቀጠል ተደራደሩ ማለታቸው ኢትዮጵያውያን ካላቸው የብዙ ዘመናት አገርን የመምራት ታሪክ አንፃር ሊቀበሉት የማይችሉት ግፊት መሆኑን ለማስረዳት ተጠቅመውበታል። በኢትዮጵያ የሰሜኑ ክፍል የወጣውን እባጭ ለማስተንፈስ በውስጥ አቅም ሕግን የማስከበር ዘመቻ ተደርጎ ወሳኝ ድል መገኘቱን አመልክተው፣ የውጭ ኃይሎች ግፊት ተገቢ አለመሆኑን አስረድተዋል።ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሃሳብ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ከሊህቅ እስከ ደቂቅ የሚደገፍ ነው። ምክንያቱ ደግሞ ግልፅ ነው። እኛ ኢትዮጵያውያን በመካከላችን የሃሳብ ልዩነት ቢኖረንም፣በአገር ሉአላዊነት ላይ የማንደራደር መሆናችን ነው። በቀጥታ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስገነዘቡት ‹‹ምንም ደሃ ብንሆን ለራሳችን ክብር አለን። የእርዳታ ፍርፋሪ ለመቀበል ሲባል በተፅእኖ ስር የምንወድቅ አይደለንም›› ምክንያቱም እኛ ኢትዮጵያውያን ነን። ሉአላዊ ነን ስንል በተግባር ትርጉሙን፤ የነፃነትን ጥልቅ ስሜትን የምንረዳ ለዚያም የሚመጥን አገረ መንግሥት ያለን ኩሩ ሕዝቦች ነን።ከዚህ መነሻ በአገራችን በመላው አካባቢ የተጀመረው ሕግ የማስከበር ዘመቻ በውስጥ አቅምና ብቃት የሚያልቅ እንጂ እንደ እርጎ ዝንብ የራሳቸውን ፍላጎት ለማሳካት በሚግተለተሉ ምኞተኞች ፍላጎት የሚፈፀም አለመሆኑ ሊታወቅ ይገባል የሚል እምነት አለኝ።ለዚህ ነው በዚህ የአጭር ቀን የሕግ የማስከበር ዘመቻ ምክንያት ኢትዮጵያውያን ጠላትና ወዳጃቸውን ለይተዋል የሚል ሃሳብ ለማንሳት የወደድኩት። ትህነግ ላለፉት 30 ዓመታት የኢትዮጵያውያንን ልብ ሰብሮ መርዙን እስኪተፋ ድረስ የልቡን እየፈፀመ የኖረ ባንዳ መሆኑ ግልፅ እንደሆነው ሁሉ፤ እርሱን አደብ ለማስገዛት በተደረገው ዘመቻ ላይ አሰላለፋቸውን ከመርዘኛው ቡድን ጋር ያደረጉ ጠላቶቻችንን ለይተንበታል። በተቃራኒው ደግሞ በትህነግ ሴራ ጠላት አድርገን ፈርጀናት የቆየናትን ኤርትራ የኢትዮጵያውያን የቁርጥ ቀን ወዳጅ መሆኗን አረጋግጠንበታል። ሉአላዊነታችን በጎውንም ክፉውንም እንድንለይ ያደረገን አጋጣሚ ያስቃኘን የነፃነታችን ምሳሌ የአንድነታችን መሠረት ነው። ለዚህ ነው ሉአላዊ ነን ስንል ዓለም በዚህ መንገድ እንዲገነዘበን የምንሻው! ሰላምአዲስ ዘመን ህዳር 29/2012", "passage_id": "d5a7dcf246e16b31c223a548e8e9e748" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፦ እኔ\nያየሁትን\nየአዲስ\nአበባን\nአውድ\nላስቃኛችሁ\nእንጂ\nበድፍን\nኢትዮጵያ\n፤\nብሎም\nበድፍን\nዓለም\nባሉ\nኢትዮጵያውያን\nዘንድ\nተመሳሳይ\nስሜት  ስለመኖሩ\nአልጠራጠርም። ጉዳዩ የታላቁ\nህዳሴ ግድባችን ጉዳይ\nነውና። አሁድ ሃምሌ 26 /2012 ዓ.ም ለወትሮው በክረምቱ ጭጋግና ዝናብ ጨለምለም የምትለው አዲስ አበባ ትናንት ያለወትሮ ባህሪዋ ፈክታለች። የአዲስ አበባ ጎዳናዎች በሰንደቅ ዓላማ ተሞሽረው መብራት በሚያበሩና የጡርንባ ድምጽ በሚያሰሙ ተሸካርካሪዎች ተጨናንቀዋል። እግረኞች ግራና ቀኝ ሆነው ፤ ሌሎችም በየበራፋቸው ላይ ቆመው የሀገርን ፍቅርና አንድነት በሚገልጹ ዘፈኖች ደስታቸውን ይገልጻሉ። አንዳንዶች ይጨፍራሉ። አንዳንዶችም ያለቅሳሉ። ብዙዎች ስሜታቸውን መቆጣጠር የቻሉ አይመስልም። ብቻ የተደበላለቁ ሰዎች ፤ የተደበላለቁ ስሜቶች ይታያሉ። እኚህ ሰዎች የጋራ ጉዳያቸው አንድ ነው። የህዳሴው ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት ይፋዊ የብስራት ቀን ፤ እና የመጨረሻን ምዕራፍ የማጠናቀቅ የቃል ኪዳን ቀን ። ይህ የዘመናት ቁጭት መልስ ያገኘበት የመጀመሪያው ምዕራፍ ብዙዎችን በደስታ አስክሯል፤ አስፈንጥዟል ፤ ቀልብ ነስቷል። መኪኖቻቸውን በባንዲራ አሸብርቀው የተለያዩ ዜማዎችን አያዜሙ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ያላቸውን አጋርነት የሚገልጹ የከተማዋ ነዋሪዎች ስሜት በቋንቋ ለመተረክ የሚመች አይደለም። ዕልልታው ፣ፌሻታው በያንዳንዱ ሰው ላይ የሚታየው ፈገግታ ፤ ፈገግታ ውስጥ ያለው ተስፋ ውብ ነው። የግንባታው አሁን ያለበት ደረጃና እውነታ ለከተማዋ ነዋሪ ከደስታ በላይ ሆኖ አምሽቷል። አብዛኛው የከተማዋ ነዋሪ ስሜቱን ለመግለጽ ቋንቋ ያገኘ አይመስልም ። ስሜቱ ተደበላልቆበታል ፤ በአንዳንዶች አይን ስር የሚታይ የእምባ እንክብል እና ሲቃ የያዘው ድምጽ ብዙ ይናገራል። በርግጥም የታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ በያንዳንዱ ዜጋ ስጋና ደም ውስጥ ስለመግባቱ ትይንቱን በማስተዋል ለሚመለከት ተጨማሪ ትርክት አያስፈልገውም ። ለኢትዮጵያውያን የአባይ ጉዳይ ሌላው ዓለም ከሚረዳው በላይ ስለመሆኑ ተጨባጭ ማሳያ ነው።ግድቡን ከኑሮው ላይ ቆጥቦ የገነባው ከመሆኑ በላይ የዘመናት የአይቻልምን ተግዳሮት ሰብሮ ይቻላል በሚል መንፈስና ቁርጠኝነት እየገነባው መሆኑ ፣ ከዛም በላይ ከብዙ አሉባልታ ቦኋላ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሱ ታላቅ እልልታው ነው። አደባባይ ወጥቶ እልል ፤ ቋንቋ አውጥቶ ኡኡ ቢል ለተመልካች እና ለሰሚ ግር የሚል አይደለም። አቶ ተመስገን ዝናቡ በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ነዋሪ ናቸው። ዕድሜያቸው ከ60 እስከ 70 ዓመት ይሆናል። ሙሉ ልብስና ከረባት አስረዋል። በላዩ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ተጎናጽፈው ከፒያሳ ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው ጎዳና ላይ በእግራቸው እየተጓዙ ድምጻቸውን ጮክ አድርገው ደስታቸውን ይገልጻሉ። አዲስ ዘመን ስለደስታቸው\nምንጭ ሲጠይቃቸው ሲቃ በተናቀቀውና\nበተቆራረጠ ድምጽ እንዲህ\nአሉ ‹‹መጀመሪያ ይችን\nቀን እንዳይ ያደረገኝ\nእግዚአብሔር ይመስገን ፤\nበእኔ ዘመን አባይ\nመገደቡና የአባቶቻችንን ቁጭት\nበእኛ በልጆቻቸው መልስ\nማግኘቱ እጅግ ደስታ\nፈጥሮብኛል፤ ዛሬ ውስጤ\nየሚንቀለቀለው የድል አድራጊነት\nስሜት ነው። የመጪው ትውልድ ተስፋና የኢትዮጵያ ትንሳኤ ያየሁት ዛሬ ነው። ከምንም በላይ በዚህ በፈተና ወቅት ሀገሬ እንዲህ ዓይነት ድል ማግኘቷ ክብርና ኩራት ነው። ይህ ክስተት በቀሪው የህዳሴው ግድብ ግንባታ ላይ አዲስ ተነሳሽነት የሚፈጥር ነው። ግብጽም ግድቡ ለእኛ ምን ማለት እንደሆነ የምትረዳው ዛሬ ነው። የኢትዮጵያ ልጆች አሁንም ከመንግስት ጎን ቆመን ግድባችንን አንጨርሰዋለን። ብልጽግናችንንም እናረጋግጣለን ሲሉ ነበር ስሜታቸውን የገለጹት አቶ ተመስገን። አሁንም ክንዳችንን አጠናክረን ግድቡን ከመጨረስ የሚከለክለን አንዳችም ነገር ሊኖር አይችልም፤ ከተባበርንና ከተደማመጥንና በሀገራችን ጉዳይ ለማንም ቀዳዳ ካልከፈትን አንሸንፋለን። ቀጣዩንም በድል እናጠናቅቃለን። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያዊነት ስሜት እና ወኔያችንን አጠናክረን መቀጠል ይጠበቅብናል። ይላል ወታደር ፍቃዱ በስሜትና በተጋጋለ ወኔ ተሞልቶ። ወጣት ሄኖክ ወርቁ መኪናቸውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አልብሰው ደስታቸውን ሲገልጹ ከነበሩ የጨርቆስ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች አንዱ ነው ። ህዳሴው ግድብ ወደ ቀደመው ማንነታችን እና ክብራችን የመለሰን የስራችን ውጤት ነው ይላል። ተባብረን ከሰራን ድህነትን ታሪክ ማድረግ እንደምንችል ያሳየንበትና ተቀናቀኞቻችንን ተስፋ ያስቆረጥንበት ልዩ ክስተት ነው ። ይህ ግድብ የዚህ ትውል አሻራ ያረፈበት እንደመሆኑ አሁንም አንድነትን በማጠናከር ሌሎች ድሎችን ማስመዝገብ ይኖርብናል። አንድነታችን የህዳሴውን ግድብ ከዳር ለማድረስ እንደረዳን ሁሉ አሁንም ያሉብንን ችግሮች በድል መወጣት የምንችለው ትልቁ አቅማችን እንደሆነም ስሜት አውርቶናል። አሁንም እስከ መጨረሻው ለማድረስ በእውቀታችን፣ በጉልበታችን ፣ በገንዘባችን ድጋፍ ማድረግ ይኖርብናል። እኔ ዛሬ ቃል ገብቻለሁ ለዚህም ነው በአደባባ ደስታዬን እየገለጽኩ ያለሁት ብሎናል። የህዳሴውን ግድብ በአንድነት አምረንና ደምቀን እንደጀመር ነው እንዲሁ እንዳማረብንና እንደደመቅን እንጨርሰዋለን ያሉት ደግሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ናቸው፤ ቀኑን አስመልክቶ በሸራተን አዲስ በተዘጋጀ መድረክ ላይ ባስተላለፉት መልእክት። ለዚህ የመጀመሪያው ዙር የውሃ ሙሌት እንኳን ደስ ያላችሁ በማለትም ቀሪውን የግድቡን ስራ አጠናቀን ወደ ናፈቅነው ስራ ለመግባት ሁሉም የተለመደው ድጋፉን ማድረግ እንደሚገባውም አመልክተዋል። ገና የቤት ስራችን\nአላለቀም ፤ አብረን\nየምንዘምትባቸው ሌሎችም ጉዳዮች አሉን\n፤ ኮቪድ 19ኝን\nመዋጋት፣ ኢኮኖሚን እንዲያገግም\nበጋራ መስራት ፣\nውስጣዊ ችግሮቻችንንና ሰላማችንን\nማስጠበቅ ሲሉም ለመላው\nህዝብ ለቀጣይ ስራና\nድል እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።\nየታላቁ ህዳሴ ግድብ\nግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ\nአስተባባሪ ብሄራዊ ምክር\nቤት ጽህፈት ቤት\nዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ\nሮማን ገብረስላሴ እንዲሁ\nእለቱን አስመልክተው ባስተላለፉት\nመልእክት ፣ ሁሉንም\nኢትዮጵያ ውያን ሀገር\nውስጥ ያለነውና በውጭ\nየምንኖር ያለምንም ልዩነት\nአንድ ሆነን በሞራል፣\nበጉልበት፣ በእውቀት የዚህ\nድል ባለቤት ሆነናል\nብለዋል። በዲፕሎማሲ በተለይም በተለያዩ ሀገራት ያሉ ምሁራንና የአረብኛ ቋንቋ ተናጋሪ ዜጎች እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አረቡን ዓለም በመሞገትና በማስረዳት ፤ ባለፉት ዓመታት ከልጅ እስከ አዋቂ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ይህንን ውጤት አግኝተናል ሲሉም ተናግረዋል። አይጀምሩትም ተብለን ጀምረናል፤\nአይችሉትም ተብለን ችለናል፤\nአይቀጥሉም ተብለን ቀጥለናል\n፤ ውሃ አትሞሉም\nተብለንም ሞልተን አሳይተናል\nበዚህም እንደምንችል ለዓለም\nእያሳየን ያለን ህዞቦች\nነን ብለዋል። መላው\nህዝብ ድጋፉን አጠናክሮ\nመቀጠል እንዳለበት ጥሪ\nአስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 27/2012 እያሱ መሰለ", "passage_id": "28597447ad734e5e6c7272abb08aa28c" } ]
ec606fbd0d3ed3b5566eb18916cbddb4
7a2be52d0f1ba4d19993aa253c06ffd2
የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻ እጩዎች
የዓለም አትሌቲክስ በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ሽልማት በሞናኮ ሊካሄድ ዛሬ አስራ አንድ ቀን ብቻ ይቀረዋል። ለሁለት ተከታታይ ዓመታት በሁለቱም ፆታ አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት ከመጀመሪያዎቹ አስር እጩዎች ውስጥ እንኳን መካተት እንዳልቻለ ይታወሳል። በተመሳሳይ ወጣትና ተስፈኛ የሆኑ ከሃያ ዓመት በታች ያሉ አትሌቶች በሚወዳደሩበት ሽልማት ዘርፍ ሁለት ወንዶችና አንድ ሴት ኢትዮጵያዊት አትሌት ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ውስጥ መካተታቸው ይታወቃል። የዓለም አትሌቲክስ ትናንት ከሰዓት በኋላ በዘንድሮው ዓመት በወንዶች የመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች ዝርዝር ይፋ አድርጓል። የመጨረሻዎቹ ሴት እጩዎችም ዛሬ የሚለዩ ይሆናል። ጆሹአ ቺፕቴጌ ባለፈው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአስር ሺ ሜትር ቻምፒዮን የሆነው ዩጋንዳዊው ጆሹአ ቺፕቴጌ የመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች መቀላቀል የቻለ ሲሆን አትሌቱ በ2019 የውድድር ዓመት ያሳየው አስደናቂ ብቃት ሽልማቱን የማሸነፍ እድል እንዳለውም አመላካች ነው። ጆሹአ አርሁስ በተካሄደው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ በውድድር ዓመቱ ትኩረት የተሰጠው አትሌት ሆኗል። ባልተጠበቀ መልኩም ጠንካራዎቹን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዳይመንድ ሊግ በማሸነፍ በአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ አሸናፊ ለመሆን በቅቷል። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮናም 26፡48፡36 የሆነ መሪ ሰዓት አስመዝግቦ በውድድር ዓመቱ ለታላቅ ስኬት እጩ መሆን ችሏል። ሳም ኬንድሪክስ አሜሪካዊው ምርኩዝ ዘላይ ሳም ኬንድሪክስ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው አስራ ሰባት ከቤት ውጪ ውድድሮች አስራ ሁለቱን በድል አጠናቋል። የውድድር ዓመቱ የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ከመሆኑ ባሻገር የዓለም ምርኩዝ ዝላይ ቻምፒዮን ነው። በአሜሪካ የምርኩዝ ዝላይ ቻምፒዮና 6 ነጥብ 06 ሜትር በመዝለል ያስመዘገበው ስኬት ለዓለም ምርጥ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻ እጩነት አብቅቶታል። ኢሉድ ኪፕቾጌ ያለፈው ዓመት የሽልማቱ አሸናፊ የሆነው ኬንያዊው የማራቶን ፈርጥ ኢሉድ ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ ሁለት ፉክክሮች ላይ ብቻ ቢታይም ያስመዘገበው ታሪክ ለመጨረሻ እጩነት አብቅቶታል። ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ የለንደን ማራቶንን ክብረወሰን በማሻሻል በ2፡02፡37 ሰዓት ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ከዚህ በላይ ግን ከወር በፊት በቬና ማራቶን የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ያሳየበት ውድድር አይዘነጋም። ኪፕቾጌ ከትጥቅ አምራች ኩባንያው ናይኪ ጋር በመሆን በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ታግዞም ቢሆን ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች ማጠናቀቅ እንደሚቻል አስመስክሯል። 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማራቶንን በማጠናቀቅ በታሪክ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆን ቢበቃም የተመዘገበው ሰዓት በዓለም ክብረወሰንነት እንዳልተያዘ ይታወሳል። ኖህ ላይልስ አሜሪካዊው የአጭር ርቀት አትሌት ኖህ ላይልስ የሁለት መቶና አራት በአራት መቶ ሜትር ዱላ ቅብብል ቻምፒዮን ነው። በሉዛን ዳይመንድ ሊግ ሁለት መቶ ሜትርን 19፡50 በሆነ ሰከንድ በማጠናቀቅ በታሪክ አራተኛው ፈጣን ሰዓት ባለቤት መሆኑም አይዘነጋም። የዳይመንድ ሊግ የመቶና ሁለት መቶ ሜትር አጠቃላይ አሸናፊ መሆኑም በመጨረሻዎቹ እጩዎች ዝርዝር ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። ካርልስተን ዋርሆልም ኖርዌያዊው የአጭር ርቀት ኮከብ አትሌት ካርልስተን ዋርሆልም በአራት መቶ ሜትር መሰናክል የዓለም ቻምፒዮን ነው። ይህ አትሌት በውድድር ዓመቱ በተለያዩ ርቀቶች በቤት ውስጥም ሆነ ከቤት ውጪ ውድድሮች ሽንፈት አልገጠመውም። ዳይመንድ ሊግን ጨምሮ የአውሮፓ ቻምፒዮን ሲሆን ያስመዘገበው 46፡92 በታሪክ ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ሆኗል። ይህም ስኬቱ ምናልባትም ከዩጋንዳዊው አትሌት ጋር ሽልማቱን ለማሸነፍ ጠንካራ ተፎካካሪ ያደርገዋል ተብሎ ይጠበቃል። አዲስ ዘመን ኅዳር 2 /2012   ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22339
[ { "passage": "ዘንድሮ ለ3ኛ ጊዜ በሚደረገው የኢቢሲ ስፖርት ሽልማት ዙሪያ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ብሮካስቲንግ ኮርፓሬሽን ዋና መስሪያ ቤት መግለጫ ተሰጥቷል፡፡መግለጫው የኢቲቪ ስፖርትና መዝናኛ ቻናል ኃላፊ የሆኑት አቶ ካሳሁን ቃሲም፣ የጣቢያው ስፖርት ክፍል ም/ኃላፊ የሆነው ጋዜጠኛ ግርማ በቀለ እና የተቋሙ የብራንዲንግና ማርኪቲንግ ኃላፊ አቶ ጋሻው በተገኙበት ተከናውኗል፡፡በ2009 ዓ.ም ጠንካራ የፉክክር መንፈስ በመፍጠር በዓለምአቀፍ ደረጃ ውጤታማ የሆኑ ስፖርተኞችን በማፍራት ረገድ ኢቢሲ የራሱን አስተዋጽኦ ለማበርከት በማሰብ በእግርኳስና በአትሌቲክስ የስፖርት ዓይነቶች በአራት ዘርፎች የተጀመረው ሽልማቱ አምና በተመሳሳይ የስፖርት ዓይነቶች ዘርፎችን ወደ አምስት በማሳደግ በሸራተን ሆቴል በተካሄደ መርሃግብር እውቅና መስጠቱ ይታወሳል፡፡ዘንድሮም በተመሳሳይ በአምስት ዘርፎች በስፓርት ባለሙያዎች፣ ምሁራንና የስፖርት ጋዜጠኞች በድምሩ ስምንት አባላት ያሉት የቴክኒክ ኮሚቴ በእግርኳስና አትሌቲክስ የስፖርት መስኮች አስር እጩዎች ቀርበው ላለፉት ወራት በአጭር የፅሁፍ መልእክት እና በፌስቡክ ድምፅ ሲያሰባስቡ መቆየታቸው ተገልጿል፡፡ከቀረቡት አስር እጩዎች መካከል በሁለቱም የስፖርት መስኮች የመጨረሻ ሦስት እጩዎች ይፋ ተደርገዋል። የመጨረሻዎቹ ሦስት እጩዎች የተለኡበትም ሂደትም 75% ከባለሙያዎች በተሰበሰበ እንዲሁም 25% ከአድማጭ ተመልካቹ በተሰበሰበ ድምፅ ስለመሆኑም ተገልጿል፡፡በዚህም መሠረት በሴቶች እግርኳስ እመቤት አዲሱ፣ ሴናፍ ዋቁማ እና ሰናይት ቦጋለ ለመጨረሻ እጩነት ሲቀርቡ በወንዶች ደግሞ አማኑኤል ገ/ሚካኤል፣ ሱራፌል ዳኛቸው እና ያሬድ ባየህ የመጨረሻ እጩዎች ሆነዋል፡፡በመጪው ጥቅምት 29 በስካይ ላይት ሆቴል በደማቅ ሁኔታ በሚካሄደው መርሃግብር አሸናፊዎቹ የሚለዩ ይሆናል። በተያያዘም በዘንድሮ የ3ኛው የኢቢሲ ስፖርት ሽልማት ላይ በኢትዮጵያ እግርኳስ ላይ በስፓርታዊ ጨዋነት ጥሩ አበርክቶ ለነበራቸው የእውቅና ምስክር ወረቀት የሚበረከት ይሆናል፡፡", "passage_id": "39f114c51477fac872444f6f4bd98d8a" }, { "passage": "በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስር በሚደረጉት ውድድሮች ጥሩ ብቃት ላሳዩ ስፖርተኞች ከ1977 ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው ሽልማት አምና በተለየ መልኩ በአንድ መድረክ ላይ መከናወን የጀመረ ሲሆን ዛሬም የ2010 ኮከቦችን ተሸላሚ አድርጓል። 03፡00 ላይ እንደሚጀመር መርሀ ግብር ተይዞለት የነበረው ሥነ ስርዓቱ 04፡40 ሲል በሰርከስ ትርዒቶች የተከፈተ ሲሆን በቅርቡ በሞት ያጣነው አሰልጣኝ ሥዩም አባተም በህሊና ፀሎት ታስቧል። በመቀጠልም የፌዴሬሽኑ ፕሬዘደንት አቶ ኢሳያስ ጂራ ተሸላሚዎችን እንኳን ደስ ያላችሁ ባሉበት የመክፈቻ ንግግር አምና የነበረው የስፖርታዊ ጨዋነት ችግር ዘንድሮ እንዳይደገም የሁሉንም ትብብር እንደሚጠይቅ አሳስበው ፕሮግራሙ በይፋ ጀምሯል።\nጥረት ኮርፖሬት ፣ አርባምንጭ ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ ከአንድ እስከ ሦስት በመሆን በተሸለሙበት የሴቶች ሁለተኛ ዲቪዚዮን ደግሞ ምስር አብርሀም ከጥረት ኮርፖሬት ኮከብ ተጫዋች ሆና ስትመረጥ የቡድን አጋሯ ታሪኳ በርገና ኮከብ ግብ ጠባቂ ፣ አሰልጣኝ ሠርክአዲስ ትዕግስቱ ደግሞ ኮከብ አሰልጣኝ ሆነዋል። በሌሎች ሽልማቶች ፎዚያ መሀመድ (ኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ) እና ምስር አብርሀም (ጥረት ኮርፖሬት) ኮከብ ግብ አግቢ መሆን ችለዋል።\n\nየመጨረሻ በነበረው ኢትዮጵያ የወንዶች ፕሪምየር ሊግ ጅማ አባ ጅፋር ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና እንደደረጃቸው ሽልማታቸውን ሲቀበሉ ተመስገን ሳሙኤል እና ብሩክ የማነብርሀን የምስጉን ረዳት ዳኛ እና የምስጉን ዋና ዳኛ ክብርን አግኝተዋል። በኮከቦች ሽልማት ደግሞ የኢቢሲ ስፖርት ሽልማት አሸናፊው የቅዱስ ጊዮርጊሱ አብዱልከሪም መሀመድ ኮከብ ተጫዋች በመሆን ሲመረጥ የጅማ አባ ጅፋሮቹ ዳንኤል አጄዬ ኮከብ ግብ ጠባቂ ፣ ኦኪኪ አፎላቢ ኮከብ ግብ አግቢ አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ደግሞ ኮከብ አሰልጣኝ በመሆን አሸንፈዋል።\n\nእንደ ቢጫ እና ቀይ ካርድ ቁጥር ባሉ የዲስፕሊን ሪከርዶች ላይ ተመስርቶ በሚደረገው የስፖርታዊ ጨዋነት ሽልማት ጅማ አባ ጅፋር ከወንዶች ፕሪምየር ሊግ አዳማ ከተማ እና ጥረት ኮርፖሬት ደግሞ ከአንደኛ እና ሁለተኛ ዲቪዚዮን የሴቶች ፕሪምየር ሊግ አሸናፊ ሆነው የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።\nበመጨረሻም በ22ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አዲስ አበባ ስታድየም ላይ መከላከያ ወልዋሎ ዓ.ዩን ባስተናገደበት ጨዋታ በተነሳው ግርግር ዋና ዳኛ እያሱ ፈንቴን ከጥቃት ለመከላከል ጥረት ያደረገው ፍፁም ገብረማርያም የስፖርታዊ ጨዋነት ልዩ ተሸላሚ መሆን ችሏል።", "passage_id": "1e79a05e2ff6132c37bd3c7edb589846" }, { "passage": "ሶከር ኢትዮጵያ ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለአዲሱ አመት 2010 በሰላም አደረሳችሁ እያለች ለሶስተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአመቱ የእግርኳስ ሰዎች/ተቋማት ሽልማትን አሰናድታለች፡፡ በዚህ ፅሁፍም ስለ ሽልማቱ ፣ የምርጫ መስፈርት ፣ እጩዎች እና ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮችን ታቀርባለች፡፡ ስለ ሽልማቱይህ ሽልማት በአንድ አመት ውስጥ በእግርኳሱ ተፅእኖ ለፈጠሩ ግለሰቦች የሚሰጥ ሽልማት ነው፡፡ በሜዳ ውስጥ ውጤታማነታቸውን ካሳዩ ባሻገር በአጠቃላይ እግርኳሱ ላይ የሚገኙ ማናቸውም ግለሰቦች በዚህ ሽልማት ውስጥ ይካተታሉ፡፡ከነዚህም መካከል\nተጫዋቾች ፣ አሰልጣኞች ፣ ዳኞች ፣ የህከምና\nባለሙያዎች ፣ የአስተዳደር ሰዎች ፣ የሚድያ ባለሙያዎች ፣ ደጋፊዎች ፣ በጎ ፍቃደኞች እና የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡በሜዳ ላይ ድንቅ አቋም የሳየ ተጫዋች ፣ ውጤታማ አመት ያሳለፉ አሰልጣኞች እና ባለሙያዎች ፣ እግርኳሱን አንድ ደረጃ ከፍ ለማድረግ አስተዋጽኦ ያደረጉ ፣ ከዚህ ቀደም ያልታየ አዲስ ነገር ያሳዩ ወይም ግኝት ያገኙ ፣ ለችግሮች መፍትሄ የሰጡ እና የመሳሰሉት ለሽልማቱ እንደ መስፈርትነት ያገለግላሉ፡፡የውድድሮች ደረጃ እና የሀገሪቱ የእግርኳስ እርከኖች ለሽልማቱ አንድ መስፈርት ናቸው፡፡ ለምሳሌ በኢንተርናሽናል ውድድር እና ከኢትዮጵያ በደረጃቸው ከፍ ባሉ የሊግ ውድድሮች ውጤታማ መሆን ፣ የብሔራዊ ቡድን ስኬት እና የሀገር ውሰጥ የሊግ እርከኖች እንደየደረጃቸው የየራሳቸው ክብደት ይኖራቸዋል፡፡ያለፉ አሸናፊዎችበ2007 በተደረገው ምርጫ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ታሪክ የመጀመርያዋ ሴት አሰልጣኝ ለመሆን የበቃችው መሰረት ማኒ አሸናፊ ሆናለች፡፡ ቀጥሎ በተካሄደው የ2008 ምርጫ ደግሞ በወንዶች እግርኳስ ዘርፍ ጌታነህ ከበደ ፤ በሴቶች እግርኳስ ደግሞ ሎዛ አበራ ሆነው ተመርጠዋል፡፡ዘርፍይህ ሽልማት በ2007 ሲጀመር ዘርፉ አንድ የነበረ ሲሆን በሁለቱም ፆታ የሚገኙ ግለሰቦች አንድ ላይ ተወዳድረዋል፡፡ በ2008 የሽልማት አመት ዘርፉ ወደ ሁለት ከፍ ብሎ በወንዶች እግርኳስ አና ሴቶች እግርኳስ በሚል ተከፍሏል፡፡ ዘንድሮ ደግሞ ዘርፉ ወደ 4 ከፍ ብሎ የወጣቶች እግርኳስ እና ተቋማት/ክለቦች ዘርፍ ለብቻቸው ሽልማት ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡የወንዶች እግርኳስበዚህ ዘርፍ በወንዶች እግርኳስ ተፅእኖ የፈጠሩ ግለሰቦች ይሸለማሉ፡፡ በሁለቱም ጾታ ያሉ ግለሰቦች በወንዶች እግርኳስ ላይ እስካሉ ድረስ አሸናፊ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡-ለምሳሌ የወንድ ቡድንን የምትመራ ሴት አሰልጣኝ በዚህ ዘርፍ ትወዳደራለች፡፡የሴቶች እግርኳስበዚህ ዘርፍ በሴቶች እግርኳስ ተፅእኖ የፈጠሩ ግለሰቦች ይሸለማሉ፡፡ በሁለቱም ጾታ ያሉ ግለሰቦች በሴቶች እግርኳስ ላይ እስካሉ ድረስ አሸናፊ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡-ለምሳሌ የሴቶች ቡድንን የሚመራ ወንድ አሰልጣኝ በዚህ ዘርፍ ይወዳደራል፡፡የወጣቶች እግርኳስበዚህ ዘርፍ ውስጥ በወጣቶች ውድድሮች ላይ ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ፣ ለወጣቶች እና ለታዳጊዎች እግርኳስ እድገት መልካም ስራ የሰሩ ፣ በእግርኳስ መጀመርያ ወቅታቸው ላይ ረጅም ርቀት መጓዝ የቻሉ ወጣቶች በዚህ ዘርፍ ይካተታሉ፡፡ክለቦች / ተቋማት ዘርፍበዚህ ዘርፍ በአመቱ ስኬታማ ጊዜ ያሳለፉ እና በእግርኳሱ የተለየ በጎ ተፅዕኖ የፈጠሩ ክለቦች ፣ በእግርኳሱ ውስጥ የጎላ ተፅእኖ የፈጠሩ ተቋማት እውቅና የሚሰጥበት ዘርፍ ነው፡፡ድምፅ አሰጣጥበዚህ ሽልማት 70% ድምጽ የሚሰጡት የሶከር ኢትዮጵያ ኤዲቶርያል አባላት ሲሆኑ የድረ ገፃችን አንባቢያን ድምፅ 30% ይይዛል፡፡ስለ እጩዎችየወንዶች እግርኳስ ዘርፍሳላዲን ሰኢድየቅዱስ ጊዮርጊሱ አጥቂ ለክለቡ ስኬታማ የውድድር አመት ትልቁን ሚና ተጫውቷል፡፡ በተለይም በካፍ ቻምፒየንስ ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ የምድብ ድልድል ውሰጥ እንዲገባ እና በምድቡም ተፎካካሪ እንዲሆን የሳላዲን 7 ጎሎች አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነበር፡፡ ፈረሰኞቹ ለ4ኛ ተከታታይ አመታት የሊጉን ዋንጫ ከፍ ሲያደርጉም ወደ ቻምፒዮንነት ለማንደርደር እጅግ ወሳኝ የሆኑትን ጎሎች ጨምሮ 15 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡ጌታነህ ከበደየአምናው የሶከር ኢትዮጵያ የአመቱ ሰዎች/ተቋማት አሸናፊ የሆነው ጌታነህ በግሉ ግሩም አመት አሳልፏል፡፡ 25 የሊግ ግቦችን በማስቆጠርም የሊጉን በአንድ የውድድር አመት በርካታ ግብ የማስቆጠር ሪኮርድ ከ16 አመታት በኋላ ሰብሯል፡፡ኡመድ ኡኩሪ ከ2007 ጀምሮ በግብጽ ሊግ እየተጫወተ የሚገኘው ኡመድ እንደዘንድሮው ስኬታማ ጊዜን አላሳለፈም፡፡ ወደ ስሞሀ ክለብ የተዛወረው ኡመድ በኤንታግ ኤል ሀርቢ የውድድር አመት ቆይታው የክለቡ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኖ አጠናቋል፡፡ሴቶች እግርኳስ ዘርፍሰናይት ቦጋለበሴቶች ፕሪምየር ሊግ ብዙዎችን ያሳመነ ምርጥ የውድድር አመት አሳልፋለች፡፡ ደደቢት ለተከታታይ አመታት የሊጉ ቻምፒዮን እና የጥሎ ማለፉ የፍጻሜ ተፋላሚ እንዲሆን የአጥቂ አማካይዋ ሰናይት ሚና የጎላ ነበር፡፡ሎዛ አበራየ2008 ” የሶከር ኢትዮጵያ የአመቱ የእግርኳስ ሰዎች/ተቋማት” ተሸላሚ የሆነችው ሎዛ ለተከታታይ 3ኛ ጊዜ የፕሪምየር ሊጉ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ደደቢትን ለቻምፒዮንነት አብቅታለች፡፡ በሴካፋ የሴቶች ዋንጫ መልካም ጊዜ ያሳለፈችው ሎዛ ወደ ቱርክ በማቅናትም የሙከራ ጊዜ በማሳለፍ ላይ ትገኛለች፡፡ዮሴፍ ገብረወልድየሀዋሳ ከተማ ሴቶች ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት ዮሴፍ ገብረወልድ በወጣቶች የተገነባ ቡድን በመስራት በሊጉ ተፎካካሪ መሎን ችሏል፡፡ በምድቡ ኢትዮጵየያ ንግድ ባንክን መፈተን የቻለው ሀዋሳ ጠንካራውና አመቱን ሙሉ ሽንፈት ያልቀመሰው ደደቢትን በመርታት የጥሎ ማለፍ ባለ ድል እንዲሆን የአሰልጣኝ ዮሴፍ አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነበር፡፡ወጣቶች እግርኳስ ዘርፍተመስገን ዳናበወጣቶች እግርኳስ ላይ ተደጋጋሚ የበላይነት እየያሳየ ከሚገኘው ሀዋሳ ከተማ ጀርባ አሰልጣኝ ተመስገን ዳና ይገኛል፡፡ በ2008 ከ17 አመት በታች ጥምር ድል ከሀዋሳ ጋር ያሳካው ተመስገን ሙሉውን ቡድን ይዞ ወደ 20 አመት በታች በመሻገር ለመጀመርያ ጊዜ የተደረገውን የ20 አመት በታች ፕሪምየር ሊግ እነና ጥሎ ማለፍ አሸናፊ እንዲሆን አስችሏል፡፡ ባለፉት አመታት ለዋናው ቡድን በርካታ ተጫዋቾችን ያበረከተው አሰልጣኝ ተመስገን ዘንድሮም በዚህ ተግባሩ ቀጥሏል፡፡ቢንያም በላይበኢትዮጵያ እግርኳስ ትልቁ መድረክ ላይ ሁለተኛ የውድድር አመቱን ያሳለፈው ቢንያም ፈጣን እድገቱን ቀጥሎ ወደ አውሮፓ ተሻግሯል፡፡ በትጋት በርካታ የሙከራ ጊዜያት በማሳለፍ በመጨረሻም ወደ አልባንያ አምርቶ በዩሮፓ ሊግ ተሳታፊ ለሆነው ስኬለንደብሩ ክለብ ፈርሟል፡፡አቡበከር ነስሩበ17 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን ጎልቶ የወጣው አቡበከር በውድድር ዘመኑ አጋማሽ ለኢትዮጵያ ቡና ዋናው ቡድን በተሰለፈበት የመጀመርያ ጨዋታ ግብ አስቆጥሮ የመወያያ ርዕስ መሆን ችሏል፡፡ የወደፊቱ የኢትዮጵያ እግርኳስ ኮከብ የመሆን እምቅ አቅም እንዳለውም በተሰለፈባቸው ጨዋታዎች አሳይቷል፡፡በተቋማት / ክለቦች ዘርፍቅዱስ ጊዮርጊስ2009 ቅዱስ ጊዮርጊስ በ81 አመት ታሪኩ ከሚጠቀሱ ስኬታማ አመታት መካከል ያሳለፈበት ሆኖ አልፏል፡፡ በክለቡ ታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ 4ኛ ተከታታይ አመታት የሊግ ቻምፒዮን ሲሆን በሀገራችን ክለቦች የቻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ምድብ ድልድል ገብቷል፡፡ ከሁሉም በላይ በክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ስም የተሰየመውና በክለቦቻችን ታሪክ የመጀመርያ የሆነው የታዳጊዎች አካዳሚን አጠናቆ ያስመረቀው በ2009 አመት ነው፡፡ኮካ ኮላበሀገሪቱ እግርኳስ ላይ እንደችግር የሚጠቀሰው ለታዳጊዎች የመጫወት እድል የሚሰጥ የውድድር እጥረትን ለመቅረፍ እየሰሩ ከሚገኙ ተቋማት መካከል ኮካ ኮላ ይጠቀሳል፡፡ እድሜያቸው ከ15 አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎችን በሁለቱም ጾታ የሚያሳትፈውና በመላ ሀገሪቱ ከ1500 በላይ ትምህርት ቤቶች 27 ሺህ ታዳጊዎችን እግርኳስ የመጫወት ህልማቸውን እንዲያሳኩ የረዳው ኮፓ ኮካ ኮላን በማዘጋጀት ኮካ ኮላ ለኢትዮጵያ እግርኳስ የበኩሉን እየወጣ ይገኛል፡፡ሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕባለፉት 10 አመታት በርካታ ቁጥር ያለው ግዙፍ ስታድየሞች እየተገነቡ ቢሆንም ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የወልድያው መሐመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ስታድየም ብቻ ነው፡፡ ይህን ዘመናዊ ስታድየም በ2009 ሙሉ ለሙሉ አጠናቆ ያስረከበውና ወጪውን ሙሉ ለሙሉ የሸፈነውም የሼህ መሐመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ድርጅት በሆነው ሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ነው፡፡", "passage_id": "6d8289d6f09669f1db6b8fee2810a3c5" }, { "passage": "በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር በተካሄዱ ስድስት የውድድር ዓይነቶች የ2011 ኮከቦች የሽልማት መርሃግብር ዛሬ ምሽቱን በካፒታል ሆቴልና ስፓ ተካሂዷል።የ2011 ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች እጩዎች ከነበረባቸው ጨዋታ መልስ በመርሃግብሩ እንዲታደሙ በማሰብ ከተያዘለት ሰዓት እጅጉን ዘግይቶ በጀመረው በዚሁ መርሃግብር በፌደሪሽኑ ስር በሚካሄዱ ውድድሮች በዓመቱ የተሻለ አፈፃፀም የነበራቸው ተጫዋቾች አሰልጣኞችና ዳኞች እውቅና የተሰጠ ሲሆን ዘንድሮ በተለየ መልኩ የህይወት ዘመን እንዲሁም ልዩ ተሸላሚዎች ተካተውበት የኢፌድሪ ስፓርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኤልያስ ሽኩር እንዲሁም የእግርኳስ ፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ ጂራን ጨምሮ በርከት ያሉ የስራአስፈፃሚ አባላት በተገኙበት በድምቀት ተካሂዷል።መርሐግብሩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ ጅራ ይህ ሽልማት ተሸላሚዎችን ለማበረታት ብቻ ሳይሆን ሌሎች ዘንድሮ በሽልማት ውስጥ ያልተካተቱት ደግሞ በቀጣይ ይበልጥ ጠንክረው በመስራት የተሻለ የውድድር መንፈስ ለመፍጠር ታልሞ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል።በሽልማት መርሐግብሩም በቅድሚያም በተለያዩ የውድድር አይነቶች በአመቱ በስፖርታዊ ጨዋነት ዘርፍ ተሸላሚዎች እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን የተዘጋጀላቸውን የምስክር ወረቀት ከክብር እንግዶቹ በክብር ተቀብለዋል።የስፖርታዊ ጨዋነት ዘርፍ አሸናፊዎችከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ – ፋሲል ከነማ\nአንደኛ ሊግ – ጋሞ ጨንቻ\nከፍተኛ ሊግ – ቡራዩ ከተማ\nሴቶች ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ዲቪዝዮን – መቐለ 70 እንደርታ\nአንደኛ ዲቪዝዮን ሴቶች – ኢትዮ ኤሌክትሪክ\nወንዶች ፕሪምየር ሊግ – ፋሲል ከነማበመቀጠል በቅደም ተከተል በየውድድሩቹ የተሻሉ ለነበሩ ስፖርተኞችና ዳኞች ሽልማት በክብር እንግዶቹ የተበረከተ ሲሆን በዚህምከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ ተሸላሚዎችየምስጋና እውቅና\n1ኛ ወላይታ ድቻ\n2ኛ መከላከያ\n3ኛ ሀዋሳ ከተማ-ምስጉን ዋና ዳኛ አብዲ ከድር\n-ምስጉን ረዳት ዳኛ መኮንን ይመር\n-ኮከብ ግብ አስቆጣሪ – ታምራት ስላስ (ወላይታ ድቻ)\n-ኮከብ ግብጠባቂ – አቡሽ አበበ (ወላይታ ድቻ)\n-ኮከብ አሰልጣኝ – ግዛቸው ጌታቸው (ወላይታ ድቻ)\n-ኮከብ ተጫዋች – መስፍን ታፈሰ (ሀዋሳ ከተማ)አንደኛ ሊግየምስጋና እውቅና\n1ኛ ባቱ ከተማ\n2ኛ ኮልፌ ቀራንዮ\n3ኛ ጋሞ ጨንቻ-ምስጉን ረዳት ዳኛ – ጌዲዮን ሄኖክ\n-ምስጉን ዋና ዳኛ – ሙሉነህ አብዲ\n-ኮከብ ጎል አስቆጣሪ – ቤዛ መድህን (ሀዲያ ሊሞ)\n-ኮከብ ግብጠባቂ – ወንድወሰን ረጋሳ (ባቱ ከተማ)\n-ኮከብ አሰልጣኝ – ቆፋ ኮርሜ (ባቱ ከተማ)\n-ኮከብ ተጫዋች – ፈቱ አብደላ (ኮልፌ ቀራንዮ)ሴቶች 2ኛ ዲቪዝዮንየምስጋና እውቅና\n1 አቃቂ ቃሊቲ\n2 መቐለ 70 እንደርታ\n3 ፋሲል ከነማ-ኮከብ ግብ አስቆጣሪ – ዓለሚቱ ድሪባ (ሻሸመኔ)፣ ዮርዳኖስ በርኸ (መቐለ)\n-ኮከብ ግብጠባቂ – ዓይናለም ሽታ (ቂርቆስ ክ/ከተማ)\n-ኮከብ አሰልጣኝ – አቡዱራህማን ዑስማን (አቃቂ ቃሊቲ)\n-ኮከብ ተጫዋች – ንግስቲ ኃይሉ (አቃቂ ቃሊቲ)ከፍተኛ ሊግየምስጋና እውቅና\n1-ሰበታ ከተማ/ወልቂጤ ከተማ/ሀዲያ ሆሳዕና\n-ምስጉን ረዳት ዳኛ – ድሪባ ቀነኒሳ\n-ምስጉን ዋና ዳኛ – ዓለማየሁ ለገሰ-ኮከብ ጎል አስቆጣሪ – ስንታየሁ መንግስቱ (አርባምንጭ ከተማ)\n-ኮከብ ግብጠባቂ – ጆርጅ ደስታ (ኢትዮጵያ መድን)\n-ኮከብ ተጫዋች – ጌቱ ኃይለማርያም (ሰበታ ከተማ)\n-ኮከብ አሰልጣኞች\nምድሀ ሀ አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና (ሰበታ ከተማ)\nምድሀ ለ አሰልጣኝ ደረጀ በላይ (ወልቂጤ ከተማ)\nምድሀ ሐ አሰልጣኝ ግርማ ታደሠ (ሀዲያ ሆሳዕና)የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አንደኛ ዲቪዝዮንየምስጋና እውቅና\n1 አዳማ ከተማ\n2 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ\n3 መከላከያ-ምስጉን ረዳት ዳኛ – ወይንሸት አበራ\n-ምስጉን ዋና ዳኛ – ፀሀይነሽ አበበ\n-ኮከብ ጎል አስቆጣሪ – ሴናፍ ዋቁማ (አዳማ ከተማ)\n-ኮከብ ግብጠባቂ – እምወድሽ ይርጋሸዋ (አዳማ ከተማ)\n-ኮከብ አሰልጣኝ – ሳሙኤል አበራ (አዳማ ከተማ)\n-ኮከብ ተጫዋች – ሴናፍ ዋቁማ (አዳማ ከተማ)የወንዶች ፕሪምየር ሊግየምስጋና እውቅና\n1 መቀለ 70 እንደርታ\n2 ሲዳማ ቡና\n3 ፋሲል ከተማ-ምስጉን ረዳት ዳኛ ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ – ትግል ግዛው\n-ምስጉን ዋና ዳኛ ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ – ቴዎድሮስ ምትኩ\n-ኮከብ ጎል አስቆጣሪ – አማኑኤል ገ/ሚካኤል (መቐለ 70 እንደርታ)\n-ኮከብ ግብጠባቂ – ፊሊፕ ኦቮኖ(መቀለ 70 እንደርታ)\n-ኮከብ አሰልጣኝ – ገብረመድህን ኃይሌ(መቐለ 70 እንደርታ)\n-ኮከብ ተጫዋች – ሱራፌል ዳኛቸው(ፋሲል ከነማ)በተጨማሪም ሀገራችንን በተለያዩ ዓለምአቀፍ ውድድሮች ላይ በዳኝነት ያስጠሩት ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ፣ ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ ፣ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ ተመስገን ሳሙኤልና እውቁ ፌዚዮቴራፒስት ይስሃቅ ሽፈራው በመርሃግብሩ ልዩ ተሸላሚ በመሆን እውቅና ተስቷቸዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ እግርኳስ አባት ለሆኑት ክብር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ የህይወት ዘመን ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ሽልማቱን የተረከቡት ልጃቸው አቶ ታደለ ይድነቃቸው ባደረጉት ንግግር አባታቸውን ዋቢ በማድረግ ዝነኛ (ተሸላሚ) መሆን ቀላል እንደሆነና ዝነኛ ሆኖ መቀጠል ከባዱ ፈተና መሆኑን በማስታወስ ለተሸላሚዎች አደራ አዘል መልእክት አስተላልፈዋል።", "passage_id": "28154695d8476256379c6e1678f61247" }, { "passage": "ውድድሩ ለወራት በድረ ገጽ ድምጽ ሲሰጥበት ቆይቶ የዘርፉ ባለሙያዎች ሙያዊ ዳኝነት ታክሎበት ፍጻሜውን አግኝቷል።\n\nየሽልማቱ አንዱ ዘርፍ በሆነው 'የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ዲዛይነር' ውድድር ደግሞ በናይሮቢ የምትኖረው ኢትዮጵያዊቷ ኮከብ ዘመድ አሸናፊ ሆናለች። \n\nባለፈው ቅዳሜ በናይሮቢ በተካሄደው የውድድሩ ማሳረጊያ መርሃ ግብር ኮከብ የፋሽን ትርዒት አቅርባ ሽልማቷንም ከአዘጋጆቹ ተቀብላለች።\n\nኮከብ ለዚህ ሽልማት ከኬንያ፣ ከሩዋንዳና ከታንዛኒያ እጩ ከሆኑ አምስት ሌሎች ዲዛይነሮች ጋር ተፎካከራለች።\n\nየሽልማቱ አላማ በኢንዱስትሪው የራሳቸውን አዲስ እይታ ተጠቅመው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ዲዛይነሮች ክብር መስጠት እንደሆነ በአዘጋጆቹ ድረገጽ ላይ ሰፍሯል። \n\nየመገምገሚያ መስፈርቶቹ ደግሞ አዳዲስ ፈጠራ ፣ ጥሩ የዲዛይን አጨራረስ፣ የግል ምልከታና ለሌሎች አርአያ መሆናቸውን ይጨምራል።\n\nኮከብ ከአውሮፓውያኑ 2009 ጀምሮ ባቋቋመችው ኮኪ ዲዛይንስ የኢትዮጵያና ሌሎች የአፍሪካ አልባሳትን እያዋሃደች የአፍሪካን ባህል በዲዛይኖቿ ታስተሳስራለች።\n\nበቅኝ ከተገዙባት ብሪታኒያ የመጣው የኬንያ ዳኞች አለባበስ የነጻነት ተምሳሌት በሆነ ካባ ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀየረው በኮኪ ዲዛይንስ ነው።\n\nበውድድሩ በ2017 በፋሽን ኢንዱስትሪ በ13 ዘርፎች ስኬት ያስመዘገቡ ተሸልመዋል\n\nየኬንያ ዳኞችን አለባበስ የቀየረች ኢትዮጵያዊት\n\nከጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ልብስ በተጨማሪ ደግሞ ሌሎች አፍሪካውያን የሚቀምሙላትን ባህላዊና ዘመናዊ ልብሶች ታዘጋጃለች።\n\nለሴቶች ፣ ለወንዶችና ለልጆች ለልዩ ዝግጅት፣ ለሥራ ቦታና ለበዓላት የሚሆኑ ንድፎችን ቀርጻ በተለያዩ የፋሽን ትርዒቶች ላይ ታሳያለች፤ ለገበያም ታቀርባለች።\n\nየኢትዮጵያን ባህላዊ የሸማ ጨርቆችና ጥለቶችን ከሌላ ዘመናዊ ጨርቅ ጋራ እያዋሃደች ለየእለት ሥራ ምቹ በሚሆን መልኩ ስታዘጋጅ ቆይታለች።\n\nበነዚህ ሁሉ ሥራዎቿ ታዲያ የምትከተለው መርህ የፋሽን ሚና 'የቀድሞውን ባህላዊ አልባሳት ከዘመኑ ጋር እያዋሃዱ የማሳደግ እንጂ እነርሱን ጥሎ በአዳዲሶች የመተካት ሊሆን አይገባም' የሚል ነው።\n\n ", "passage_id": "7a4ea8dbcb8a6ddf1cbb031afe55af40" } ]
73135cb98dda5480d6eef5474e12840c
36de16f6420f08fdee4e34e6b9e963f8
“በትግራይ ተጨማሪ የጅምላ መቃብር መገኘቱ አይቀርም” ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አስታወቁ
በጋዜጣው ሪፖርተሮች አዲስ አበባ፡- ባለፉት አስርት ዓመታት የህወሓት ጁንታ የተለያ የፖለቲካ አመለካከትና አቋም ያላቸውን የትግራይ ተወላጆች በጭካኔ ሲገድል ከመቆየቱ ጋር በተያያዘ በክልሉ ተጨማሪ በርካታ የጅምላ መቃብሮች መገኘታቸው አይቀርም ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ነጋሲ በየነ ተናገሩ።የኢትዮ-አሜሪካ ሲቪክ ካውንስል እና የኢትዮጵያዊያን ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ባዘጋጁት የዌብናር ውይይት ላይ የተሳተፉት አቶ ነጋሲ በየነ እንደተናገሩት፤ ጁንታው ስርዓቱን ያዋቀረው ከአልባኒያ ኮሚኒዚም በመኮረጅ ወዳጅና ጠላት በሚል ሲሆን፤ ከእርሱ ውጪ ያለን አስተሳሰብና አቋም የሚያራምዱ ግለሰቦችንና ቡድኖችን ባለመቀበል ሲያስርና ሲገድል ኖሯል። በመሆኑም በትግራይ ክልል በቅርቡ ተጨማሪ የጅምላ መቃብር መገኘቱ አይቀርም። የህወሓት ጁንታ በ17 ዓመቱ የሽምቅ ውጊያ ወቅት በድርድር ሰበብ የጠራቸውን የትግራይ ነፃነት ግንባር (TLF) አመራሮችን ራት ጋብዞ ሌሊት በተኙበት እንደገደላቸው ያስታወሱት አቶ ነጋሲ፤ በተመሳሳይ አሁንም በመከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ አባላት ላይ የፈጸማቸው ክህደትና ግፍ የቡድኑ ተፈጥሯዊ ባህሪ ስለሆነ ዓለም ሊረዳውና ሊያወግዘው ይገባል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ ከተደረገው የፖለቲካ ለውጥ በኋላ ኩርፊያ ውስጥ የገባው ጁንታው ለልማትና ለመልካም አስተዳደር ዞር ብሎ አይቶት የማያውቀው የትግራይ ህዝብ ጉያ ውስጥ ገብቶ ተደብቆ ቆይቷል ያሉት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ፤ ለፖለቲካ ስልጣን ጥሙ ሲል የትግራይ ህዝብ በጠላቶች እንደተከበበ እንዲሰማው ለማድረግ ሲደክም ቆይቷል፤ በሰዎች መካከልም ፍርሐትን ለመጫን ሞክሯል፤ ራሱንም ብቸኛ የትግራይ ህዝብ ተከላካይ አድርጎ አሳይቷል ነው ያሉት። ከለውጡ በኋላም ወደ ትግራይ የተመለሰው የህወሓት ጁንታ ለትግራይ ወጣቶች ምንም ዓይነት የተሻለ የሥራ ዕድል አልፈጠረም፤ ይልቁንም ወጣቱን በልዩ ኃይል ስም እያሰባሰበ ሲያሰለጥን ምሽግ ሲያስገነባ መቆየቱን ነው ያብራሩት። በዚሁ ዌብናር ላይ የተሳተፉትና የውይይቱ አስተባባሪ አንድነት እምሩ እንደተናገሩት፤ ጁንታው ከውድቀት ለመዳን በተለያዩ ማህበራዊ ገጾች ላይ ከፍተኛ የሐሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት ሕብረተሰቡን ለማወናበድና ኢትዮጵያን ለመበተን ከፍተኛ ጥረት ማድረጉን ማረጋገጥ እንደቻሉ አስረድተዋል፡፡ጁንታው በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በሁሉም የሰሜን እዝ ላይ እና ሁሉም ወታደራዊ ካምፖች ላይ የተቀናጀ ጥቃት መፈጸሙን ያነሱት አቶ አንድነት፤ ጁንታው ጥቃቱን የፈጸመበትን እቅድ ባለማሳካቱ፤ ሐሰተኛና የፈጠራ መረጃዎች በመንዛት በሌላ የጥፋት መንገድ ተጠምዶ እንደነበር ማረጋገጥ እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ እቅዱም ከውድቀት ሊታደገው አልቻለም ሲሉ ነው ያስረዱት።ጁንታው በሕግ ማስከበሩ ሂደት በተወሰደበት ዕርምጃ ላይነሳ ተንኮታኩቷል፤ በመሆኑም እየሸሸ ሲሄድ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ንጹሐን ዜጎችን ሕይወት ከማጥፋቱም ባለፈ በሺዎች የሚቆጠሩትን ደግሞ ለማገት ሞክሮ በሁሉም ረገድ ለሽንፈት መዳረጉን አቶ አንድነት ለተሳታፊዎቹ አብራርተዋል። የአሜሪካ ሴኔት አባላት፣ የምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነት ሠራተኞች፣ የአፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪዎች፣ የሃሳብ አመንጪዎች (ቲንክ ታንክ) እና ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን በተደረገው ገለጻ መሳተፋቸው ተገልጿል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 8 2013/ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37523
[ { "passage": "የግንቦት ሃያን 29ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ጊዜ እጅግ አሳሳቢ መሆኑንና በኢህአዴግ ዘመን “ተጨብጠው ነበር” ያላቸው ፖለቲካዊ፣ ምጣኔኃብታዊ፣ ማኅበራዊና ዓለም አቀፍ ስኬቶች መቀልበሳቸውን፤ አልያም እያሽቆለቆሉ መሆናቸውን በመግለፅ በከበዱ ቃላትና አቀራረብ ተችቷል።“ሃገሪቱ ገደል አፋፍ ላይ ትገኛለች” ብሏል።ይህ መግለጫና ፌደራል መንግሥቱም የሰጡት ምላሽ በምልዓት ተዘግበዋል።ለመሆኑ በክልሉ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎችና ህዝብስ ምን ይላሉ? ማነጋገር ጀምረናል። የትግራይ ሕዝብ ያለበት የድኅነት ክብደት “ከማንኛውም ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የባሰ ነው፣ የበረታ ጭቆናም አለበት” ሲሉ የአረና ትግራይ ለዴሞክራሲና ለሉዓላዊነት አመራር አባላት አቶ ገብሩ አሥራት እና አቶ አምዶም ገብረሥላሴ ተናግረዋል።ሁለቱም ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የግንቦት ሃያን 29ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ያወጣውን መግለጫ “የተጋነነ” ብለውታል።ከዚህ መግቢያ ጋር የተያያዘው ከአቶ ገብሩ አሥራት ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ የተካሄደው ከጥቂት ሣምንታት በፊት ነበር። በራዲዮ ዝግጅታችን ቀደም ሲል በከፊል ቢስተናገድም ሙሉው ቃለ ምልልስ በገፆቻችን ላይ ሳይወጣ ቆይቷል። ያዳምጡት።በነገራችን ላይ፣ የትግራይን ክልላዊ መንግሥት ተጨማሪ ማብራሪያና ሃሣብ ለመጠየቅ ከክልሉ ፕሬዚዳንት አንስቶ በተለያዩ ደረጃዎች ያሉ ባለሥልጣናትን ለማግኘት በስልክና በቴክስት መልዕክት በተደጋጋሚ ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሣካም። \n ", "passage_id": "90e22f4ace66d8af7afe3bfdf2435bab" }, { "passage": " የ200 ሰዎች የጅምላ መቃብር በሶማሌና በኦሮሚያ ክልል አዋሣኝ አካባቢ መገኘቱን የገለፀው የፌደራል ፖሊስ፤ በጅምላ ተቀብረው የተገኙትን አስከሬኖቹ ማንነት ለመለየት እያደረገ ምርመራ እያደረገ መሆኑም አስታውቋል፡፡ ፖሊስ የጅምላ መቃብሩን ያገኘው በአሁን ወቅት በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ መሐመድ ኡመር ላይ ተጨማሪ ምርመራዎች በሚያከናወንበት ወቅት መሆኑን ጠቁሟል፡፡ በሰዎች ግድያና ኢ-ሠብአዊ ድርጊቶች በመፈፀም ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት አቶ አብዲ መሐመድ፤ በሥልጣን ላይ በቆዩባቸው ላለፉት 13 አመታት በክልሉ በርካታ ኢ-ሠብአዊ ተግባራት በዜጐች ላይ መፈፀማቸውን ዓለምአቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማት በተለያዩ ጊዜያት ባወጧቸው ሪፖርቶች መጠቆማቸው ይታወሳል፡፡ አሁን ፖሊስ አግኝቸዋለሁ ያለው የጅምላ መቃብር አቶ አብዲና አስተዳደራቸው ከሚወቀሱባቸው የሰብአዊ መብት ጥሰት ጋር ስለመያያዙ ተጣርቶ ውጤቱ ለፍ/ቤት እንደሚቀርብ ታውቋል፡፡ በግድያ፣ በአስገድዶ መድፈርና ዜጐችን በተለያየ ዘዴ ማሰቃየትና ቶርች መፈፀም ወንጀል ተጠርጥረው ጉዳያቸው እየተጣራ የሚገኘው የቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት፤ ከትናንት በስቲያ ፍ/ቤት ቀርበው ተጨማሪ የአሥራ አራት ቀን ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡   ", "passage_id": "9d0e599f8f0c450d636001505cdf36b5" }, { "passage": "የህወሓት ቡድን በሁመራ አቅራቢያ በምትገኘው ማይካድራ ከተማ በአማራ ተወላጆች ላይ አሰቃቂ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈፅሟል ሲል የክልሉ ገዥ ፓርቲ አስታወቀ።የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ትናንት ባወጣው መግለጫ እንዳለው ህወሓት ግድያውን የፈፀመው በህዝቦች መካከል የእርስ በርስ ጦርነት/ሲቪል ዋር/ እንዲቀሰቀስ ለማድረግ ነው።ድርጊቱ በዓለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የሚያስጠይቅ ወንጀል መሆኑን እናምናለን ብለዋል በመግለጫው የተጠቀሱት አዲሱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር።\n", "passage_id": "5253e80bd450a1fb3b0bef685241d2ec" }, { "passage": "የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አገልግሎቶች ትግራይ ውስጥ በሚካሄደው ውጊያ ምክንያት እየተሰቃዩ ያሉትን በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመርዳት እንዳልቻሉ ገልፀዋል።የኢትዮጵያ መንግሥት ወደ ክልሉ ሰብዓዊ ረድኤት እንዲገባ መተላለፊያ መስመር እስዲከፈት እስካልፈቀደ ድረስ የሚሰቃዩትን ለመርዳት እንደማይችሉ የሰብዓዊ ረድኤት አገልግሎቶቹ መናገራቸውን የአሜሪካ ድምጽ ዘጋቢ ሊሳሽ ላይን ዘገባ ይጠቁማል።\n", "passage_id": "e988ebc429c469620a41d5b7e89c815a" }, { "passage": "የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ በባህርዳር፣ ጎንደር፣ ዳንሻ፣ ሁመራና ማይካድራ ከተሞች የመጀመሪያውን ዙር የመስክ ምልከታ ማድረጉን ገልጾ፣ በአከባቢው “በጁንታው” የሕወሓት ቡድን የተፈጸመውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት አብራርቷል፡፡\n\"የጁንታው ቡድን\" በሁመራና በማይካድራ ከተሞች የአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ ትኩረት በማድረግ እጅግ ዘግናኝ ጭፍጨፋ ማድረጉን ቦርዱ በሪፖርቱ አካቷል፡፡\nበተለይ በማይካድራ በአሰቃቂ መንገድ ተገድለው የተገኙ ሰዎች ቁጥር 700 እንደሚደርስ ፣ ነገር ግን በየጫካው እስካሁን ያልተገኙ አስከሬኖች ሊኖሩ እንደሚችሉና በዚህም የሟቾቹ ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ለማ ተሰማ ጠቁመዋል፡፡\n\"ሳምሪ\" የተባለው የወጣቶች ቡድን ይህንን አሰቃቂ ወንጀል ቢፈጽምም ፣ በአንጻሩ የትግራይ ተወላጅ ከሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ገዳዩ ቡድን ሲያሳድዳቸው የነበሩ ሰዎችን በቤታቸው፣ በቤተክርስቲያንና በእርሻ ቦታዎች በመደበቅ የብዙ ሰዎች ህይወት እንዲተርፍ ማድረጋቸውን መርማሪ ቦርዱ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡\nበዳንሻ የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት ቤተሰቦችን በማፈን እንግልት እንደተፈጸመባቸውም ነው ሪፖርቱ የጠቆመው፡፡\n\"ከሃዲው ቡድን\" ለጥፋት ያሰለፋቸውና በመንግስት ቁጥጥር ስር የዋሉ የትግራይ ልዩ ሃይልና የሚሊሻ አባላት\nሰብኣዊ አያያዝ እየተደረገላቸው መሆኑንም መርማሪ ቦርዱ አስረድቷል፡፡\nቦርዱ ጉብኝቱን የጀመረባቸው የባህርዳርና የጎንደር የሲቪል አየር ማረፍያዎች ላይ የደረሰው ጉዳት አነስተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በከተሞቹ በሚገኙ ሆስፒታሎች ለመከላከያ ሰራዊትም ሆነ \"ከሃዲው ቡድን\" ለጥፋት አሰልፏቸው ለቆሰሉ የትግራይ ልዩ ሃይልና ሚሊሻ አባላት ተመሳሳይ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ለማ ተሰማ አስረድተዋል፡፡\nአያይዘውም የጎንደር ከተማ ማህበረሰብና የከተማ መስተዳድሩ ታካሚዎቹን በመንከባከባቸው፤ እንዲሁም ከሀዲው የህወሃት ቡድን ባደረሰባቸው ጥቃት ከትግራይ ክልል በመሰደድ በከተማዋ ለተጠለሉ ተፈናቃዮች ሰብኣዊ ድጋፍ ስለማድረጋቸው አመስግነዋል፡፡\nመሪማሪ ቦርዱ በቀጣይነት በመንግስት ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን ያስቀመጠ ሲሆን፣ ወንጀለኞቹን የማደኑ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና በሱዳን ድንበር አከባቢ ሌላ አደጋ እንዳይፈጠር ጥንቃቄ እንዲደረግ በማለት አሳስቧል፡፡\nበህክምና ላይ ከሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መካከል የባንክ ደብተርና ሌሎች ማስረጃዎች የጠፋባቸው ስለሚገኙ መፍትሄ እንዲሰጥ፣ የተበታተኑ የመከላከያ ሰራዊት ቤተሰቦች እንዲገናኙ ቢመቻች እንዲሁም የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ያለውን በጀት ለተፈጠረው ድንገተኛ አደጋ አሟጦ በመጠቀሙ ድጎማ ቢደረግለት የሚሉ ምክረ ሃሳቦች በመርማሪ ቦርዱ ተሰጥቷል፡፡\nመርማሪ ቦርዱ በቀጣይ ወደ ራያ፣ አላማጣ፣ ሽሬ፣ አክሱም፣ መቀሌና በሌሎች አከባቢዎች ተገኝቶ የምርመራ ስራውን እንደሚያከናውን የቦርዱ ሰብሳቢ ጠቁመዋል፡፡\nዘገባውን ያገኘነው ከሕ/ተ/ም/ቤት የፌስቡክ ገጽ ነው፡፡\n", "passage_id": "91ffd50657b0d548257eafcf0e855ea8" } ]
4cfca7c18057291d1913d8df5bd3b728
d5741accc7522818cda29642327ddec8
“የትግራይ ወጣት ራሱን ከነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስማማት ወደ ኃላፊነት ሊመጣ፣ ሃገሩንና ህዝቡንም ሊያገለግል ይገባል” – አቶ ነብዩ ስሑልሚካኤል የትግራይ ብልጽግና ጽህፈት ቤት ኃላፊ
እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ የትግራይ ወጣት የጁንታው ቡድን ማንንም የማይወክል መሆኑን በመረዳት ራሱን ከነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስማማት ወደኃላፊነት በመምጣት ሃገሩንና ህዝቡን እንዲያገለግል የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ጥሪ አቀረበ። የጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ነብዩ ስሑልሚካኤል ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ውድቀት የትግራይ ህዝብም ሆነ ወጣት ውድቀት ሳይሆን የራሱ የጁንታው ብቻ ነው። በመሆኑም ወጣቱ በተፈጠረው ነገር መቆዘም ሳይሆን በተፈጠረው ትልቅ ዕድል በመጠቀም ወደ ኃላፊነት መምጣት፣ አገሩንና ህዝቡንም ለማገልገል መዘጋጀት ይጠበቅበታል። እንደ አቶ ነብዩ ገለጻ፤ አንዳንድ ወጣቶች የህወሓት ጁንታ ቡድን ውድቀት እነርሱንም አብሮ የሚጥላቸው ስለሚመስላቸው በቁዘማ ውስጥ ገብተው ይታያሉ። ሊያውቁት የሚገባው እውነት ግን የህወሓት ጁንታ ከወጣቱ፣ ከህዝቡ፣ ከመንግሥትና ከተለያዩ አካላት ብዙ ምክርና ዕድል ተሰጥቶት አልጠቀምም ብሎ በራሱ እብደትና ቅሌት ለዚህ ማብቃቱ ሲሆን፤ የጁንታው ውድቀትም ከትግራይ ወጣቶችም ሆነ ከማንኛውም ትግራዋይ ጋር የማይገናኝ መሆኑ ነው። ይልቁንም የሆነ ቡድን በራሱ መንገድ ብቻ እያየ ሲሄድ የጠፋ አድርጎ መውሰዱ ይገባል። ለጁንታው ቡድን ምክርና ሃሳብ ካዋጡ አካላት አንዱ  የትግራይ ወጣት መሆኑን የገለጹት አቶ ነብዩ፤ “ምከረው ምከረው እምቢ ካለ መከራ ይምከረው” እንደሚባለው ሁሉ አሁን ላይ ጁንታው በራሱ መንገድ ተጉዞ የጠፋ እንደመሆኑ ወጣቱ ለዚህ ቡድን ምንም ማድረግ አይችልም። ስለዚህ ወጣቱ የጁንታው ቡድን ማንንም የማይወክል መሆኑን በመረዳት ራሱን ከነባራዊ ሁኔታ ጋር አስማምቶ መቀጠል እንደሚጠበቅበት ጠቁመዋል። በሌላ በኩልም ወጣቱ ለውጡ የራሱ እንደሆነ በመረዳት ይህንን ደማቅ ምዕራፍ እውን አድርጎ ለራሱም ተጠቃሚ የሚሆንበት፣ ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ሁኔታ አገሩንም ህዝቡንም የሚያገለግልበትን ዕድል በአግባቡ ሊጠቀም፤ ከአንዳንድ አላስፈላጊ ቁዘማዎችና መፋዘዞችም ሊላቀቅ እንደሚገባው አቶ ነብዩ አሳስበዋል። የጁንታው መወገድ ለትግራይ ህዝብ የነፃነት ቀኑ ተብሎ ሊጠቀስ የሚገባው ነው ያሉት አቶ ነብዩ፤ የታገለላቸው የዴሞክራሲ፣ የልማት እና የእኩል ተጠቃሚነት ዓላማዎች ተሳክተው የሚያይበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑንም አብራርተዋል። በተለይም አዲሱ ትውልድ “እኛ ብቻ እናውቅልሃለን” ከሚለው አካል የተላቀቀበት እንደመሆኑ፤ አሁን ባገኘው ዕድል ተጠቅሞ የራሱን አስተዋጽዖ እንዲያበረክትና ወደ ኃላፊነት መጥቶ ህዝቡን እንዲያገለግል የሚያስችለው ጊዜ በመሆኑ አጋጣሚውን እንደ ወርቃማ ጊዜ ሊመለከተው እንደሚገባም መክረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ9/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37582
[ { "passage": " ወጣቱ ትውልድ በታጋዮች ለተከፈለው መስዋዕት ተገቢውን ክብር በመስጠት አሁን አገሪቷ ለምትፈልገው የልማት ትግል ዝግጁ ሊሆን እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮነን አሳስቡ።የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) 40ኛው ዓመት የምስረታ በዓል “ትናንት፣ ዛሬና ነገ ዋስትናችንና ኃይላችን ህዝባዊ መስመር ህወሓት/ኢህአዴግ ነው” በሚል መሪ ቃል ዛሬ ተከብሯል።ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደመቀ በበዓሉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ህወሓት/ኢህአዴግ ላለፉት 40 ዓመታት በከፈለው ከባድ መስዋዕት አሁን ያለው ሠላም፣ ዴሞክራሲና ፈጣን እድገት መመዝገብ ችሏል።“በመቶ ሺዎች ለሚቀጠሩ ወጣቶች ሞትና ቁስለት ምክንያተ የሆነውን የኢትዮጵያ ህዝቦች ትግል ወጣቱ ትውልድ ለተከፈለው መስዋዕት ተገቢውን ክብር በመስጠት ለኢትዮጵያ ህዳሴ ስኬት ሊቆም ”ይገባል ብለዋል።“የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች መብቶች ያስከበረ የህውሓትና የትግራይ ህዝብ የከፈሉትን መራራ ትግል የህዳሴው ጉዞ ዳር ለማድረስ ልንጠቀምበትና ልንማርበት ይገባል” ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ።“በዓሉ ያሉብንን የመልካም አስተዳደርና የኪራይ ሰብሳቢነት ችግሮች ቆራጥነትና ህዝባዊነት በተላበሰ መልኩ የአሁኑ ትውልደ እንዲታገል መልእክት የሚተላለፍበት ክቡር ቀን ነው” ብለዋል።የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ ምክትል ሊቀመንበር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በበኩሉቸው ትግሉ ብሄራዊ ጭቆና ሙሉ በሙሉ ከደርግ ሥርዓት ጋር በመቅበር ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ በራሳቸው የሚወስኑበት መድረክ መፍጠር ችሏል።ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ባለፉት ሥርዓቶች የነበሩትን የገዢዎች ምክር ቤቶች ወደ ህዝቦች ምክር ቤትነት በመቀየር በአንድነትና በመከባበር የሚመክሩበት ዕድል አግኝተዋል።ምክር-ቤቶቹ አሁን ለወከላቸው ህዝብ ብቻ ሳይሆን የሰማዕታት አደራ ጭምር በኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም ዶክተር ደብረጽዮን ጠይቀዋል።የህወሓት ነባር ታጋይ አቶ ስብሓተ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት “በተሰራው የትግል ታሪክ እንድንኩራራና እንድንቀመጥ ሳይሆን እንድንማርበት ሊሆን ይገባል።”“በታሪክ መኖር የለብንም” ያሉት ታጋይ ስብሓት “ለተገኘው ሠላምና ዴሞክራሲ አደጋ የሆኑትን ጠባበነትና ትምክህተኝነት የመታገያ ስልት የምንማርበት የኢትዮጵያ ህዝቦች የትግል ታሪክ ሊሆን ይገባል” ብለዋል።“የህወሓት/ኢህአዴግ 50ኛውን ዓመት በዓልን ስናከብር የኢትዮጵያ ህዳሴ ተረጋግጦ ማየት ያስፈልጋል” ነው ያሉት።የትግሉ አጀማመር፣ የድሉ ሚስጢርና ከትግሉ በኋላ ድርጅቱ ያስመዘገባቸው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስኬቶች የሚቃኝ ጽሁፍ በታጋይ ዓባይ ፀሃየ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።በበዓሉ የህዝብ ተወካዮችና የፌደሬሽን ምክርቤት አባላትና አጋር ድርጅቶች ተገኝቷል።(ኢዜአ)", "passage_id": "07a75cdffdf91f8349b2cf6bd890d079" }, { "passage": "\"ጦርነት ለማስቀረት ስንል ኃይል በማጠናከር ተዘጋጅተናል\" ብለዋል የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል።\"የፌደራል መንግሥት ሥልጣን የያዘ ሃይል በትግራይ ህዝብ ላይ ሲፈፅመው የነበረውን ሴራ ወደ ኃይል እርምጃ በማሸጋገር ላይ ስለሆነ የክልሉ ህዝብ ዝግጅቱን አጠናክሮ መቀጠል አለበት\" ብለዋል ለክልሉ መገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ።የሀገሪቱን ችግር ለመፍታት ሁሉን አቀፍ መድረክ መዘጋጀት አለበት ሲሉ አክለዋል።\n", "passage_id": "5567b17ade347d2912e59741109aef57" }, { "passage": "ወጣቱ በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ ኃይል በመሆኑ ተጠቃሚነቱን ይበልጥ ማረጋገጥ እንደሚገባ ጽህፈት ቤቱ ለዋልታ በላከው መግለጫ ገልጿል፡፡መንግስት የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ  በርካታ ፕሮግራሞችንና ፓኬጆችን ቀርጾ መንቀሳቀሱን ጽህፍት ቤቱ አስገንዝቧል፡፡ በመሆኑም በመጀመሪያው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን በሚሊዮን የሚቆጠር ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ በተያዘው የዕቅድ ዘመንም የተሻለ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡በመግለጫው እንደተመለከተው በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በተገነቡት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ወጣቶች ተጠቃሚ መሆን ችለዋል። በመንግስት ግዙፍ ፕሮጀክቶች ውስጥ በተፈጠረ በሚሊዮን የሚቆጠር የሥራ ዕድል 840 ሺ የሚጠጉ ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ተጠቃሚ ሆነዋል። ከ39 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር ተፈጥሮላቸዋል።ወጣቶች በኃይል ማመንጫዎች፣ በባቡር መስመር ዝርጋታ፣ በመንገድ ግንባታ፣ በስኳርና   በማዳበሪያ ፋብሪካዎች ላይ ተቀጥረው እየሰሩ ነው፡፡ ይህም ገቢያቸውን ከማሳደግ በተጨማሪ የቴክኖሎጂ ሽግግር በመፍጠርና ዕውቀትን ለመቅሰም እንደሚረዳቸው ጽህፈት ቤቱ አስገንዝቧል፡፡ከ34 በላይ በሚሆኑ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ብቻ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ወጣቶች ከመጀመሪያ እስከ ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተከታተሉ መሆኑን መግለጫው አትቷል፡፡ በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት ከመቀጠር በተጨማሪ ወጣቶች በአነስተኛና ጥቃቅን ተደራጅተው ሥራ እንዲፈጥሩ መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ነው ብሏል መግለጫው፡፡ወጣቶች በተለወጠ አስተሳሰብና በባለቤትነት መንፈስ በመንቀሳቀስ፤ ችግሮቻቸውን በጋራና በተደራጀ አግባብ በመፍታት ለተጀመረው ልማት የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጽህፈት ቤቱ አሳስቧል፡፡ ህብረተሰቡም ከመንግስት ጎን በመሰለፍ የበኩሉን እንዲወጣ ጽህፈት ቤቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡", "passage_id": "32548220c6b552f72c2eb1fa08d4edcc" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- ‹‹እኔም ሆንኩ የምመራው የብልጽግና ፓርቲ የትግራይን ህዝብ እንደ ዋነኛ አጋሩና አካሉ ያስባል›› ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንት\nየብልጽግናን ፓርቲ ከተቀላቀሉ\nየትግራይ ክልል ተወላጆች\nጋር በተወያዩበት ወቅት፤\nምሁራኑን ወክለው ጥያቄ\nያቀረቡት የትግራይ ክልል\nየብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ\nአመራር ዶክተር አብረሃም\nበላይ፤ የትግራይ ክልል\nተወላጅ ወታደራዊና ሲቪል\nባለሥልጣናት እስርን፣ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን፣\nየጸጥታና የደኅንነት ስጋቶችን\nየተመለከቱ ጥያቄዎች አቅርበውላቸው\nምላሽ በሰጡበት ወቅት\nከትግራይ ህዝብ ጋር\nበመሆን የኢትዮጵያን ህዝብ\nችግር በመፍታት ብልጽግናን እንደሚያረጋግጡና እርሳቸውም ሆኑ የሚመሩት ፓርቲ የትግራይን ህዝብ እንደ ዋነኛ አጋሩና አካሉ እንደሚያስብ ተናግረዋል፡፡ዶክተር አብረሃም እስር\nየሚፈጸመው የትግራይ ተወላጆች\nላይ ብቻ ነው\nበማለት በህዝብ ዘንድ\nቅሬታና የመጠቃት ስሜት\nእንዲፈጠር ማድረጉን አስታውሰው፤ አፍራሽ ሃይሎች ስለ ለውጡና በለውጡ ምክንያት ስለመጣው አዲስ አስተሳሰብ ሕዝቡ ለነገ በትኩረት እንዳይሰራ በማድረግ የትግራይ ህዝብ በፌዴራል መንግሥቱ ይልቁንም በለውጥ ኃይሉ እምነት እንዳይኖረው የሚያደርጉትን አፍ ለማዘጋት በትኩረት እንዲሰራ ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹‹የፌዴራል መንግሥት የትግራይ ክልል መንግሥትን እንደ ሁለተኛ ዜጋ ለአንዲት ሰከንድ አስቦ አያውቅም ። አብረው የነበሩ ሰዎችም በዚህ ረገድ የሚያሳማን ሀሳብ እንደሌለ ጠንቅቀው ያውቃሉ። የትግራይን ህዝብ ያገለለ መንግሥት የማንንም ጥቅም አያስከብርም። ህዝብ እንዲከፋፈልና እንዲለያይ የሚያደርግ መንግሥት ኢትዮጵያን ጥቅም አልባ ያደርጋል። ህዝብን ገፍቶ ልማትና ብልጽግናን ማምጣት አይቻልም፤ ብዙዎቹም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ልብ እየገዙ ይመለሳሉ ››ብለዋል። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ወታደርም ሲቪልም ሆነው በእስር ላይ ያሉ የሁሉም አካባቢ ተወላጆች ናቸው፤ በአሁኑ ወቅት ያለው የእስረኛ ቁጥር ዝቅተኛ ነው፤ የተለየ የሙስና ችግር ኖሮ መረጃ ተገኝቶባቸው የፍርድ ሂደት ላይ ያሉ ሰዎች ካልሆኑ በስተቀር ከህግ አንጻር ክፍተት የማያመጡና በህግ አግባብ ሊታዩ የሚችሉ ጉዳዮችን ዓቃቤ ህግ በፍጥነት እልባት እንዲሰጥ ይደረጋል ። በተቻለ መጠን ህዝቡን ሊያረጋጋ የሚችልና የፖለቲካውን ምህዳር ሊያሰፋ የሚችል ውሳኔ በመንግሥት በኩል ለመውሰድ ዝግጁነት አለ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ወንጀል ሳይሰራ እስር ቤት የሚገባ እንደሌለ በመጥቀስ ‹‹ነገር ግን አሁን ባለው ባህል ከአንድ አካባቢ ሰው ሲታሰር ‹እኛ ታሰርን› በሚል ሁሉም የራሱን ያነሳል። ሆኖም ወንጀለኛን ከብሄር ጋር ማገናኘት ተገቢ አይደለም›› ብለዋል። የኢኮኖሚ ጉዳይን በሚመለከት ትግራይ ሳይለማ ሌላውን አካባቢ ማልማት እንደማይቻልና የበጀት ክፍፍሉም ለሁሉም ክልሎች ፍትሐዊ አሠራርን በተከተለ መንገድ መሰራቱን ገልጸው፤ ይህ ሂደት እንደሚቀጥልና የአገሪቷ ኢኮኖሚ ሲጨምር በጀት እንደሚጨምር አመላክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የትግራይ\nህዝብ ከፌዴራል መንግሥትና\nከጎረቤት አገራት ጥቃት\nሊመጣ ይችላል በሚል\nስጋት ውስጥ እንደሚገኝና\nመፍትሄው ምን እንደሆነ\nለተጠየቁት ሲመልሱ፤ በትግራይ\nሀዝብ ላይ ምንም\nአይነት ጫና አለመኖሩን፤\nህዝቡ ባለመብትና የአገሩ\nባለቤት እንደመሆኑ መጠን\nከየትኛውም አቅጣጫ የትግራይን\nህዝብ የሚያሰጋ ጥቃት\nእንደሌለና ከዚህ ቀደም\nበኢትዮጵያ ጥቃት ሲሰነዘር\nሁሉም ኢትዮጵያዊ የጋራ\nጥቃት አድርጎ መከላከሉን\nበማስታወስ፤ ወደ ፊትም\nይህ ሁኔታ እንደሚቀጥል\nገልጸው፤ ጥቃት ቢታሰብ\nበቂ የሆነና ሉዓላዊነትን\nየሚያስጠብቅ ሀይል መኖሩን\nጠቁመዋል።አዲስ ዘመን የካቲት 11/2012አዲሱ ገረመው", "passage_id": "fa08a59301ace2000274890779108495" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የትግራይ ህዝብ ሰላሙን ለማናጋት ከሚሰሩ ሃይሎች ራሱን ሊጠብቅና ሊታገላቸው እንደሚገባ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ ገለጹ።የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።በመግለጫቸውም የትግራይ ክልል ህዝብ የተለያዩ የሃሰት አሉባልታዎችን እየነዙ ሰላሙን ሊያናጉ የሚሞክሩ አካላትን ሊታገላቸው እንደሚገባ ጠይቀዋል።ህዝቡ “በሬ ወለደ” ወሬዎችን እያናፈሱ ሰላሙን ለማናጋት ከሚሰሩ ሃይሎች ራሱን ሊጠብቅና ሊታገላቸው ይገባልም ነው ያሉት።በአሁኑ ጊዜ አብዛኛው የትግራይ ክልል የተረጋጋ መሆኑን ያሥረዱት ዋና ስራ አስፈጻሚው ህዝቡ ምንም አይነት ስጋት እንዳይገባው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ትናንት በሙስናና በዝምድና ህዝቡን ሲያሰቃዩ የነበሩ ግለሰቦች ዛሬም በሌላ ተግባር ወንጀል የሚፈጽሙ ከሆነ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ህጋዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን ገልጸዋል።የትግራይ ክልል ህዝብ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከዴሞክራሲውም ሆነ ከልማቱ ተጠቃሚ ሳይሆን የህወሓት ቡድን የራሱ መጠቀሚያ ሲያደርገው መቆየቱን አስታውሰዋል።በመሆኑም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ለትግራይ ህዝብ እውነተኛ ዴሞክራሲ እና ተጠቃሚነት ለመስራት ዝግጁ በመሆኑ ህዝቡ የጀመረውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።ወንጀለኛውን የህወሓት ጁንታ ይዞ ለህግ ለማቅረብ በሚደረገው ጥረት ህዝቡ እንዲተባበር ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።", "passage_id": "e5fb6693ef003143e883e5bc407431e0" } ]
eedef5358a4a95f4467e365fe7087958
fcc0f34bea0812aa0b58a0cac4420d6a
ኮሚሽኑ በበጀት ዓመቱ አራት ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ለመሳብ አቅዶ እየሠራ መሆኑን ገለጸ
ሞገስ ጸጋዬአዲስ አበባ፡- በበጀት ዓመቱ አራት ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከኢንቨስተሮች ለመሳብ አቅዶ እየሠራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ። ኪሚሽኑ፣ ከአሜሪካና ከካናዳ ባለሀብቶች እንዲሁም ከሚሽነሪዎች ጋር በሃያት ሪጅንሲ ሆቴል ትናንት ተወያይቷል። ውይይቱ ላይ የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳንኤል ተሬሳ እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት በርካታ ባለሀብቶችን በመሳብ ከአራት ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንዲለማ እየተሠራ ነው። እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ የኢንቨስትመንት ህግ መሻሻሉ በኢኮኖሚው ላይ ብዙ ለውጦች እያመጣ ነው። በርካታ የአሜሪካና የካናዳ ባለሀበቶች በአዲስ መልክ በአዳዲስ ዘርፎች ላይ መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ጥናት እያደረጉ ነው። ከዚህ በፊት በተለያዩ ዘርፎች ተሰማርተው ሲያለሙ የነበሩ ባለሀብቶችም ተጨማሪ ዘርፎች ላይ ለመሰማራት አማራጮችን እየተመለከቱ ነው። በተለይ በተሻሻለው የኢንቨስትመንት ህግ በርካታ ዘርፎቸን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት አድርጓል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያን በኢንቨስተሮች ተመራጭ ያደርጋታል። ዝግ የነበሩ የኢንቨርስትመንት ዘርፎችን ክፍት መደረጉ ለማልማት ፍላጎት እያላቸው ያልቻሉ ባለሀብቶችን ወደ ዘርፉ እንዲቀላቀሉ ያደርጋል ያሉት አቶ ዳንኤል፤ ፍላጎት ያላቸው የአሜሪካና የካናዳ ባለሀብቶች ለመሰማራት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢንቨስትመንት ህጉ መሻሻሉ በምሥራቅ አፍሪካ ያለንን የኢንቭስትመንት ተመራጭነት ለማስቀጠል ይጠቅማል ያሉት አቶ ዳንኤል፤ ምቹ ሁኔታዎችን በማሳወቅ ባለሀብቶች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው እንዲያለሙ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ የኮቪድን ተጽዕኖ ከፍተኛ በመሆኑ መንግሥት ካምፓኒዎች እንዳይጎዱ በማለት የተለያዩ ድጎማዎችን ሲያደርግ ነበር። እንዲሁም ወደ ውጭ ሲልኩ ለነበሩ ድርጅቶች በሀገር ውስጥ እንዲሸጡና የገንዘብ ዕርዳታ እንዲያገኙ በማድግ ሊዘጉ የሚችሉ ድርጅቶች ሳይዘጉና ሠራተኞቻቸውን ሳይበትኑ መቆየት ችለዋል። በቀጣይም ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሥራት እቅዶችን ለማሳካትና አልሚዎችን በምቹ ሁኔታ እንዲሠሩ ለማድረግ በርካታ ቅድመ ሁኔታዎች እተሠሩ ነው። የበርዳን አማካሪ ድርጅት ማናጀር የሆኑት ትዕግስት ገረመው በበኩላቸው እንዳሉት፤ የተሻሻለው የኢንቨስትመንት ህግ ለባለሀብቶች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። ሆኖም በኢንቨስትሮች ላይ ሁሌም ይነሳ የነበረውን የግብር ችግር ለመፍታት ኮሚሽኑ ከሚመለከታቸው አከላት ጋር ቢሠራ በጣም ጥሩ ነው። እንዲሁም ከመሬት ይዞታና ከባንኮች ጋር መሠራት ቢቻል ኢትዮጵያን በቀላሉ ተመራጭ ማደረግ ይቻላል። አልሚዎች በምን ዘርፍ መሳተፍ እንዳለባቸው የሚያሳዩ ማስታወቂያዎች ቢኖሩ በርካታ ኢንቨስተሮችን መሳብ ይቻላል ያሉት ማናጀሯ፤ ከምንም በላይ ደግሞ አዳዲስ ዘርፎች ለውጭ ባለሀብቶች መፈቀዳቸው ጥሩና አበረታች ነው። ኢንቨስተሮች በመጡ ቁጥር ለሀገር ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስለሚኖራቸው መንግሥት ከአማካሪ ድርጅቶች ጋር በጋራ ሊሠራ ይገባል ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37590
[ { "passage": "ድሬዳዋ፡- መንግሥት በቱሪዝም ዘርፍ ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ይበልጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ:: በዓለም ለ40ኛ ፣ በአገራችን ደግሞ ለ32ኛ ጊዜ ትናንት በድሬዳዋ\nየቱሪዝም ቀን ላይ በተከበረበት ወቅት የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ቡዜና አልከድር እንደተናገሩት፤ መንግሥት\nየዜጎችን ሕይወት ለመቀየር የኢኮኖሚ ሪፎርም እቅድ አውጥቶ እየተንቀሳቀሰ ነው:: ቱሪዝም ለኢኮኖሚ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ በተለይ\nለውጭ ምንዛሬና ለዜጎች የሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ በመሆኑ የኢኮኖሚው እቅድ ማሻሻያ አካል አድርጎ ሥራዎች በመሰራት ላይ ይገኛሉ::\nለአብነትም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የመሪ ጥበብ የቤተመንግሥት ፕሮጀክትና የሸገር የወንዝ ዳር ማስዋብ ፕሮጀክቶች በቱሪዝም\nዘርፍ ኢኮኖሚውን ከሚደግፉ መካከል ዋነኞቹ መሆናቸውን ጠቅሰዋል:: ሁለቱ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ትልቅ ገጽታ የሚገነቡና የኢኮኖሚ\nምንጭ እንደሚሆኑ፤ ለዜጎች የሥራ ፈጠራም እንደሚያገለግሉ የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ ሚኒስቴር መስሪያቤቱም ለዘርፉ እንቅፋት የሚሆኑ\nማነቆዎችን ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አንስተዋል:: በቀጣይም በዘርፉ መነቃቃትን ለመፍጠርና የተሻለ ገቢ እንዲገኝ እየተሰራ\nእንደሆነም ተናግረዋል:: ከባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከርም አዳዲስ የኢኮኖሚ ምንጮች ለመፍጠር ይሰራል ብለዋል:: ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፉ የሚፈለገውን ያህል እየተጠቀመች እንዳልሆነ\nየሚያነሱት ወይዘሮ ቡዜና፤ ኅብረተሰቡ ለቱሪዝም ዘርፉ የሚሰጠው ግምት አናሳ በመሆኑ የቱሪዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እንደሚሰራ\nገልጸዋል:: ቱሪዝም የአገሪቱ ትልቅ አጀንዳ በሆነበት ጊዜ የቱሪዝም ቀኑ ለ32ኛ ጊዜ መከበሩ የቱሪዝም ችግሮችን በመፍታት፣አቅጣጫዎችን\nበማመላከት የቱሪዝም ሀብቶቻችን በአግባቡ ታውቀው እንዲጎበኙ ያደርጋል ብለዋል:: የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አህመድ አህመድ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤\nየንግድ ማዕከል በሆነችው ድሬዳዋ ከተማ የቱሪዝም ቀኑ መከበሩና በቱሪዝሙ ዘርፍ ድሬዳዋን ትኩረት ሰጥቶ እንድትሳተፍ ማድረጉ መከባበር፤\nእንግዳ ተቀባይነትና አንጻራዊ ሰላም ባለበትና ልማቱ በከተማዋ እንዲመጣ አስችሏል:: በተለይ ወጣቶችና ሴቶች በተፈጠረላቸው ቋሚና\nተንቀሳቃሽ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ችለዋል:: በቀጣይም ለኢንዱስትሪውና ለቱሪዝም ዘርፉ ትኩረት በመስጠት ወጣቶችንና ሴቶችን\nይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሰራ ይሆናል:: በአላይንስ ፍራንስ ትምህርት ቤት የፎቶ ኤግዚቢሽን እየተካሄደ ሲሆን፤\nበዓሉም እስከ ጥቅምት አንድ ድረስ በተለያዩ መንገዶች እንደሚከበር ታውቋል:: በተያዘው በጀት ዓመትም በዘርፉ ከ75 ሺ በላይ ለሚሆኑ\nዜጎቸ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑ ታውቋል።አዲስ ዘመን መስከረም 18/2012 ዓ.ምጌትነት ምህረቴ ", "passage_id": "95f796448fc7213b53398a14ef713061" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 9 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ግማሽ ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለፀ።", "passage_id": "2be2efb81c20a895563238dba01f5a12" }, { "passage": "፡- ከአገራዊ የ100 ቀናት ዕቅድ ውስጥ 60 በመቶ ያህል ሥራውን ማከናወን እንደቻለ የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ተቋሙ  የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻል፣ በማዘመንና ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑም ጠቁሟል፡፡ኮሚሽነሩ አቶ በዛብህ ገብረየስ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ቀልጣፋና ውጤታማ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት በመዘርጋት አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል የመጀመሪያው ቁልፍ ሥራው ነው፡፡ ይህን ለማድረግም ቀደም ሲል የነበረው የሲቪል ሰርቪስ አሠራርና አካሄድ በመልካም ገጽታው የሚታወቅበትን ሁኔታ ማስተካከል መነሻ ሥራ ሲሆን፤ በቀሪ ቀናትም አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመንና የተሳለጠ ለማድረግ እየተሠራ ነው፡፡ቀደም ሲል የነበረውን የውጤት ተኮር መመዘኛ ስርዓት በተለይም አብዛኞቹ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ወረቀት የሚበዛባቸው፣ ለመረዳት ግልጽ አይደሉም፣ ሥራዎቹ ውስብስብ ናቸው፣ የሚሉና መሠል ችግሮች ይነሱ እንደነበር ኮሚሽነሩ አስታውሰው፤ እነዚህን ችግሮች ለመፍታትም ቀላል የአሠራር ስርዓቶችን ለመዘርጋት የተቀናጀ የመረጃ ስርዓት ፕሮጀክት ላይ የሚሠሩ ፓኬጆች በየተቋማቱ ላይ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም100 በሚሆኑ የመንግሥት ተቋማት ውስጥ እየተተገበሩ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፍኖተ ካርታ ቀርፆ መተግበር ሌላው ተግባር ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ይህ ቁልፍ  ተግባር ከዓለም ባንክና ከእንግሊዝ ተቋም ጋር ግንኙነት በመፍጠር የውጭ አገር ባለሙያዎችን በማምጣት የፍኖተ ካርታ ምሰሶዎች ላይ ያተኮረ መድረክ ተዘጋጅቷል ብለዋል፡፡ ከ60 በላይ      ባለሙያዎች፣ የቢሮ ኃላፊዎች፣ በሥራው ላይ ከፍተኛ ዕውቀት አላቸው የሚባሉ አካላት ከዓለም ባንክ ባለሙያዎች ጋር በመሆን መነሻ እያዘጋጁ እንደሆነና የጥራት ማረጋገጥና ተገቢ ግብዓቶችን ሰጥቶ ወደ ተግባር የማስገቢያ ዐውደ ጥናት ለአንድ ቀን እንደሚካድ ጠቁመዋል፡፡ ፍኖተ ካርታውም ረቂቅ ተዘጋጅቶ በቀሪ አንድ ወር ውስጥ ተጠናቅቆ የሕዝብ ውይይት ይደረግበታል፡፡እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ የሰው ሀብት ልማትና አመራር ስርዓትን ማዘመን ሌላው ተግባር ሲሆን፤ በዚህም አገር አቀፍ የሰው ሀብት ልማት ፖሊሲና ስትራተጂ ሰነድ እየተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡ የሚወጡ መመሪያዎች፣ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች ሁሉ የነበረውን ችግር በሚቀርፍና በአሁኑ ወቅት የተጀመረውን አገራዊ ለውጥ በሚደግፍ አግባብ እየተሠራ እንደሆነም አብራርተዋል፡፡በተለይም የመንግሥት አሠራር በግልጽነት፣ ተጠያቂነትና በፍትሐዊነት ላይ እንዲሆንና የእነዚህ ድምር ውጤትም ሰላምን ያሰፍናል በሚል እየተሠራም ነው ያሉት ኮሚሽነር በዛብህ በዚህም አዳዲስ ምሩቃንን ወደ ሲቪል ሰርቪሱ የሚገቡበት የምልመላ ስርዓት መዘርጋት በመቶ ቀናት ውስጥ በትኩረት የሚሠራበት ነው ብለዋል፡፡ ወጣቶች ከዩኒቨርሲቲ ጀምሮ ወደ ሲቪል ሰርቪሱ የሚገቡበት ሁኔታ የሚመቻችበትና ተማሪዎቹ ገና በትምህርት ቤት ሳሉ ቀድመው ወደ ሥራ የሚገቡበትን ሁኔታ ለማከናወን ልምዱ ካላቸው ተቋማት ጋር ትስስር መፈጠሩን አብራርተዋል፡፡የሥራ ምዘናና ደረጃ አሰጣጥ (ጂኤጂ) በሁሉም የአገሪቱ ተቋማት ውስጥ ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ማድረግ በመቶ ቀናት ውስጥ የታቀደ ሲሆን፤ 99 በመቶ ያህል መጠናቀቁን አቶ በዛብህ ጠቁመዋል፡፡ አገር አቀፍ የሰው ሀብት ልማትና ሥራ አመራር ማደራጀት ጋር ተያይዞም ለረጅም ዓመታት በተቋሙ ያሉ የሌሎች መስሪያ ቤቶች መረጃዎችንም የማጠናቀር ሥራ ዘመናዊ በሆነ መንገድ የመያዝና የወረቀት ሰነዶችን ቦታ በማስለቀቅ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የመተካት ሥራ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ እስከአሁን 12 ሺህ 800 ሰነዶች በዚህ መልኩ ተስተናግደዋል፡፡ ይህም በዕቅድ የተያዘው በመቶ ቀናት ውስጥ ካሉት 100 ሺህ በላይ ሰነዶች 25 ሺህ የሚሆነውን መሥራት ነበር፡፡ ከኦዲት ጋር ተያይዞ ያሉ ሥራዎችን ደግሞ ያሉትን ሥራዎች በመቶ ቀናት ውስጥ ሊያልቅ የማይችል መሆኑ በመገምገሙ ይህን የሚሠራ የፕሮጀከት ጽህፈት ቤት ሊከፈት እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ በሥራው ላይ ያጋጠሙ ችግሮች እንዳሉም ኮሚሽነሩ አልሸሸጉም፡፡ ከተቋማት በተለይም ከዩኒቨርሲቲዎች የሚመጡ በርካታ ቅሬታዎችን ማድመጥ በርካታ ስትራተጂካዊ ጉዳዮችን በሚፈለገው ደረጃ ላለማየት ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡ እንደ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ያሉ የፈረሱ ተቋማት ሥራዎች ማጠናቀቅ፣ ተጠሪ ተቋማት በተለይ የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ የመልካም አስተዳደር ችግር ነበር በሚል የሠራተኛውና የአመራሩ መስተጋብር ጥሩ አለመሆንና መሰል ችግሮች በሥራው ያጋጠሙና ጎታች የነበሩ ምክንያቶች ነበሩ፡፡ ነገር ግን ለችግሮች መፍትሔ በማስቀመጥ በመሠራቱ ተጨባጭ ውጤት መጥቷል በማለት ሥራዎችንም በቀሪ ቀናት ለመተግበር በትኩረት እተሠራ እንደሆነ አመላክተዋል፡፡አዲስ ዘመን ጥር 1/2011", "passage_id": "311c7267a355c3a7be8059e468a629b6" }, { "passage": "የፖለቲካ ለውጡን ወደ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለመቀየር እየሠራ መሆኑን የኦሮሚያ  ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ ።የኦሮሚያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ረሺድ መሐመድ እንደገለጹት በዋናነት የግል ባለሃብቱንና የመንግሥት ቅንጅታዊ አሠራርን ለማሻሻል ውጤታማ ሥራን ለማከናወን  አተኩሮ  እየሠራ  ይገኛል ።ምክትል ኮሚሽነሩ እንደገለጹት ባለፉት ጥቂት ዓመታት የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው በተወሰነ መልኩ  ተቀዛቅዟል ።ሆኖም ባለፉት 8 ወራት በኦሮሚያ ክልል የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ማሻሻሉን  ምክትል  ኮሚሽነሩ አንስተዋል ።አሁን በኦሮሚያ ክልሉ ያለው የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴም በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ  ወደ የተሻለ  ደረጃ  ሊሸጋገርም  እንደሚችል ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል ።ቀደም ሲል  ጥቂት ግለሰቦች የክልሉን  መሬት  ወደ ራሳቸው  የመሰብሰብ ሁኔታ  ይታይባቸው ነበር ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ አሁን ይሄን በመቀየር  አርሶአደሩ የልማቱ ባለድርሻ  የሚሆንበትን  አሠራር  ተዘርግቷል ብለዋል ምክትል ኮሚሽነሩ ።በተዘጋጀው መድረክ ላይ  ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት አቶ ነዋይ መገርሳ  እንደገለጹት በተለያዩ አገራት የልማት  ሥራዎች  ላይ የቅንጅታዊ  አሠራሮች   የተለመዱ መሆናቸውንና ክልሉ አሁን  በዘርፉ  የጀመረው አሠራር  ውጤታማ  እንደሚያደርገው ምክትል ኮሚሽነሩ አብራርተዋል ።በክልሉ በኢንቨስትመንት ዘርፍ የአገልግሎት አሠጣጥ ዙሪያ የሚስተዋሉትን ችግሮች ለመቅረፍ  የሚያስችሉ ተግባራትም  እየተከናወኑ  መሆናቸው ተገልጿል ።", "passage_id": "1aa2cd4d02ea38b773f45308f97c6247" }, { "passage": "የኢኮኖሚ ዕድገቱን በተመለከተ ለመገምገም የሚያስችል ሙሉ መረጃ በአሁኑ ሰዓት ለማጠናቀር እንዳልተቻለ የፕላንና ልማት ኮሚሽን ጠቆመ፡፡ኮሚሽኑ ትናንት ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የ10 ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት እንዳስታወቀው የ2011 በጀት ዓመት አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን በተመለከተ ለመገምገም የሚያስችል ሙሉ መረጃ በአሁኑ ሰዓት ለማጠናከር ያልተቻለ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት የግል ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ አዝማሚያ፤የካፒታል በጀት አፈፃፀም ፤ የኮንስትራክሽን በጀት አጠቃቀም፤ የመካከለኛና ከፍተኛ ማኑፋክቸሪንግ ንዑስ ዘርፍ ግምታዊ አመለካከቶች አዝማሚያ ፤የመኸር ወቅት የዋና ዋና ሰብሎች ምርት ትንበያ፤ የፋይናንስ ኢንዱስትሪ አፋፃፀም እና የአገልግሎት ዘርፎችን አጠቃቀም ላይ በማተኮር ለ2011ዓ.ም በጀት ዓመት የተቀመጠውን 11.0 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ግብ ማሳካት እንደማይቻል በሪፖርቱ ላይ አብራርቷል፡፡ከታህሳስ ወር ጀምሮ ከታየው የዋጋ ግሽበት ጋር በተያያዘ በሪፖርቱ እንተገለፀው በ2011 ዓ .ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የአጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 16.2 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡የዋጋ ግሽበቱን ለማረጋጋት ኮሚሽኑ ትኩረት በመስጠት በቅርቡ ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ ከግብርና ሚኒስቴር፣ ከማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ፣ ከብሔራዊ ባንክ፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር ከተውጣጡ የስራ ሀላፊዎች ጋር የጥናት ግብረ ሀይል በማዋቀር በፕላንና ልማት ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ሰብሳቢነት የዋጋ ግሽበቱን መንስኤዎች በማጥናት ለማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ የመፍትሄ ሀሳብ ለማቅረብ በእንቅስቃሴ ላይ መሆኑ በሪፖርቱ ላይ ተገልጿል፡፡የፕላንና ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ፍፁም አስፋው እነዚህንና ሌሎች ኮሚሽኑ በ10 ወራት ውስጥ ያከናወናቸውን ተግባራት ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ከቋሚ ኮሚቴውና ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽን ሰተዋል፡፡ሀይማኖት ከበደ", "passage_id": "42cb6e04667938e26a3f238551403f38" } ]
cc01f85c5b5966ebba1abb351c8f391d
090ae3ed5bacd8bac7552b67e74c4e06
የአንጋፋው የኪነ ጥበብ ባለሙያ የአርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ከትናንት በስቲያ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አንጋፋው የኪነ ጥበብ ባለሙያ ተባባሪ ፕሮፌሰር አርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ ቀብር ሥነስርዓት ዛሬ ተፈጽሟል።ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሰሰ የህይወት ታሪክ እንደሚያስረዳው፤ በቀድሞው ሐረርጌ ክፍለ ሀገር ጎሮጉቱ በሚባል አካባቢ ከአባቱ ከአቶ ገሰሰ ቆለጭ እና ከእናቱ ወይዘሮ በለጥሻቸው ያየህይራድ መስከረም 17 ቀን 1929 ዓ.ም ነው የተወለደው። በስምንት ዓመት ዕድሜው በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የገባ ሲሆን፤ በትምህርት ቤቱ ስካውት ተሳትፎ ነበረው።በልጅነቱም ደራሲ ከበደ ሚካኤል በደረሱት “የትንቢት ቀጠሮ” ቴአትር ላይ የሚያለቅስ ሕፃን ልጅ ገጸ ባህሪይ ተላብሶ ተጫውቷል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር (በወቅቱ መጠሪያው የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ቴአትር ቤት) ከመጽሐፍ ቅዱስ የኢዮብን ታሪክ በመውሰድ በተዘጋጀ ተውኔት በመሪ ተዋናይነት የተጫወተ ሲሆን፤ በተውኔቱ ዳይሬክተር ጋባዥነት ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ አርቲስት ተስፋዬ ሲተውን ተመልክተዋል። አርቲስቱ በመሪ ተዋናይነት የተጫወተበት ይህ ተውኔት ወደ ቴአትር ሙያ እንዲገባ በር የከፈተለት እንደሆነም ይነገራል።አርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ በልጅ እንዳልካቸው መኮንን ወደ ፈረንሳይ ተልከው የሕግ ትምህርት ይማሩ ተብለው ከተመለመሉ ሰዎች እንዱ የነበረ ሲሆን የእሱም ፍላጎት የሕግ ትምህርት መማር ነበር። ይሁንና ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ኢትዮጵያ በቴአትርና ስነ ጥበብ ብዙ ባለሙያዎች ስለሌሏት ውጭ አገር በዚሁ ዘርፍ ብትማር ይሻላል ብለው በወቅቱ ለአርቲስቱ ያቀረቡለትን ጥያቄ ተቀብሏል። በ1951 ዓ.ም በጄነራል ሂውማነቲስ የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘ ሲሆን፤ በ1953 ዓ.ም በኖርዝዌስተርን ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ትምህርት ቤትም ተመርቋል። አርቲስቱ በ1954 ዓ.ም ወደ አገሩ በመመለስ በቴአትር ሙያው መሥራቱን ቀጥሏል። ወደ አገሩ ከተመለሰ በኋላ በሙያው ቴአትር መሥራትና ማዘጋጀት የጀመረ ሲሆን፤ “የሺ፣ እቃው፣ ፀረ ኮሎኒያሊስት፣ ተሃድሶ፣ “Cherchez Les Femmes” እና “ፍርዱ ለእናንተ” የተሰኙ ቴአትሮችን አዘጋጅቷል። በተለይም በ1968 ዓ.ም የደርግ ስርዓትን በሚተቸው “እቃው” ቴአትር ምክንያት በዋና ዳይሬክተርነት ተሹሞ ይሠራበት ከነበረው የአገር ፍቅር ቴአትር ቤት ታግዶ ለእስር ተዳርጓል። በፀረ-ኮሎኒያሊስትና ተሃድሶ ቴአትሮቹ በፖለቲካ ጉዳይ ያነሳቸው ሃሳቦች አወዛጋቢ እንደነበሩም ይገለጻል። አርቲስቱ የብሔራዊ ቴአትር ቤት ዳይሬክተር ሆኖም አገልግሏል።አርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ በ2010 ዓ.ም “የመጨረሽታ መጀመርታ” የተሰኘ ታሪክና ሕይወት ቀመስ ሽሙጥ ልቦለድ መጽሐፍ ለንባብ አብቅቷል። በዘመኑ የኡመር ካያምን ሩቢያቶች የግጥም መድበልን ጨምሮ በርካታ ድርሰቶች፣ ትርጉሞችና የተውኔት ጽሑፎችንም ለንባብ አብቅቷል። የቴአትር ምሁር፣ ተዋናይ፣ ደራሲ፣ መምህር፣ ተመራማሪና ተርጓሚ ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሰሰ በሙያው ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ቴአትር መሰረት የጣለና ባለሙያዎችንም ያፈራ እንደሆነ ይነገርለታል።አገር ወዳድ፣ ቅን፣ ታታሪና በሰዎች ስኬት የሚደሰት እንደሆነም የቅርብ ወዳጆቹና የሙያ አጋሮቹ ይመሰክራሉ። ተባባሪ ፕሮፌሰር አርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ የሦስት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች አባት የነበረ ሲሆን 10 የልጅ ልጆችንም አይቷል። የአርቲስቱ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ወዳጅ ዘመዶቹ የሙያ አድናቂዎቹና የሥራ ባልደረቦቹ በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል፤ ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37592
[ { "passage": "ድምፃዊ ታምራት ደስታ ከዚህ አለም በሞት ተለየ።ድምፃዊ ታምራት በድንገተኛ አደጋ ህይዎቱ  በዛሬው  ዕለት ማለፉ የተገለጸው።ታምራት ደስታ አንለያይም፣ ሃኪሜ ነሽ፣ ከዛ ሰፈር፣ ካንች አይበልጥ፣ ሊጀማምረኝ ነው እና ሌሎችም ስራዎቹ በሙዚቃ አድማጮች ዘንድ ተወዳጆች ናቸው።ድምፃዊ ታምራት ደስታ ባለትዳርና የ5 ልጆች አባት ነበር።ዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን   ኮርፖሬት ለቤተሰቦቹና ለአድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል።", "passage_id": "9ab732052f6e7cef31491ac570ea2458" }, { "passage": "ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ እና የቀድሞዋ ቀዳማዊ እመቤት ሮማን ተስፋዬ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የወርቅና ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ ተበረከተላቸው፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያምና ባለቤታቸው ትናንት በብሄራዊ ቤተመንግስት በተደረገ የሽኝት ፕሮግራም ነው ሽልማቱ የተበረከተላቸው፡፡በስነስርዓቱ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ የሀገሪቱን እድገት በማስቀጠልና በተለያዩ ሀገራዊና አለማቀፋዊ መድረኮች በመገኘት የሃገሪቱን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማጠናከራቸውን አስታውቀዋል፡፡ለአፍሪካ ምሳሌ በሚሆን መልኩ ሰላማዊ የስልጣን ርክክብ  በማድርጋቸውም  አድናቆታቸውን  ገልጸዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ  ˝አቶ  ኃይለማሪያም ደሳለኝ ማገልገልን ያወረሱን ታላቅና ጀግና መሪ ናቸው˝ ብለዋል፡፡አቶ ኃይለማሪያም በበኩላቸው ለተደረገላቸው የምስጋናና የሽኝት ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ህዝብ፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለካቢኔ አባላቶቻቸው፣ ለመንግሰት ሰራተኞችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡የተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ ወደኋላ እንዳይቀለበስ ህብረተሰቡ ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር  አብይ ድጋፍ እንዲያደርግ እና ጊዜ እንዲሰጣቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡(ኢዜአ) ", "passage_id": "1788b09c57e28c03476cba0db5e7cb15" }, { "passage": " አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአንጋፋው የማስታወቂያ ባለሙያ አቶ ውብሸት ወርቃለማሁ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ። የቀብር ስነ ስርዓቱ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመድ፣ የስራ አጋሮቻቸው እና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት ዛሬ 9 ሰዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል።አቶ ወብሸት ባደረባቸው ህመም በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው ባሳለፍነው ቅዳሜ ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት።በኢትዮጵያ የማስታወቂያ ኢንዱስትሪ ውስጥ ፈር ቀዳጅ የነበሩት አቶ ውብሸት፥ በሃገር ፍቅር ቴአትር ቤት ቴአትሮችን እንዲሁም የቴሌቪዥን ድራማዎችን በመፃፍ እና በመተወን የጥበብ ጎራውን መቀላቀላቸው ይነገራል።በመቀጠልም አንበሳ የተባለ የማስታወቂያ ድርጅት በመክፈት በዘርፉ ሲሰሩ ቆይተዋል።በተጨማሪም አቶ ውብሸት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አባል በመሆን ሀገራቸውን በመወከል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማሻሻሉ ረገድ የድርሻቸውን ተወጥተዋል።", "passage_id": "244ca0bd4db5d3df46d45dc859427d80" }, { "passage": "በትምህርት ዘርፍ በተለይም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ከ45 ዓመታት በላይ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት በአስተማሪነት፣ በዲንነትና በተመራማሪነት ያገለገሉት ዶ/ር ገሠሠ ታደሰ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ፡፡የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማዕከል የቦርድ ሊቀመንበር፣ በአእምሮ ዕድገት ውስንነት ላይ የሚሠራው አህጉራዊው ድርጅት ኢንክሉሽን አፍሪካ (Inclusion Africa) ፕሬዚዳንት የነበሩት ዶ/ር ገሠሠ ያረፉት ታኅሣሥ 19 ቀን 2008 ዓ.ም. በድንገት ሲሆን ሥርዓተ ቀብራቸው ታኅሣሥ 21 ቀን በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ዶ/ር ገሠሠ ገጸ ታሪካቸው እንደሚያመለክተው፣ በ1962 ዓ.ም. በወልዲያ፣ ከ1963 እስከ 1971 ዓ.ም. በይርጋለም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በአዲስ አበባ ቅድስት ሥላሴ የእንግሊዝኛ መምህር የነበሩ ሲሆን ከ1972 እስከ 1997 በኮተቤ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ በመምህርነት፣ በተማሪ ዲንነት፣ በኮሌጅ ዲንነት፣ የምርምርና ሕትመት ኃላፊነት አገልግለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ1997 ዓ.ም. እስካረፉበት ዕለት ድረስ በመምህርነትና ተመራማሪነት ያገለገሉ ሲሆን፣ በቋንቋዎች ጥናት ተቋምም ዲን ነበሩ፡፡ከሙያቸው ባሻገር በማኅበራዊ ኃላፊነት በተለይ በአካል ጉዳተኞችና በአእምሮ ዕድገት ውስንነትን በተመለከተ በአገራዊና አህጉራዊ ተቋማት ውስጥ በከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል፡፡በሕፃናት፣ በወጣቶችና በጎልማሶች አካል ጉዳተኞች ላይ የሚሠራው የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማዕከል የቦርድ ሊቀመንበር የነበሩት ዶ/ር ገሠሠ፣ በአፍሪካ ደረጃ በአካል ጉዳተኞች ሰብአዊ መብት ዙሪያ የሚሠራው ኢንክሉሽን አፍሪካ (Inclusion Africa) ፕሬዚዳንት ነበሩ፡፡ከአባታቸው ከሃምሳ አለቃ ታደሰ ሰጠኝና ከእናታቸው ከወ/ሮ የሺ ወዳጆ ሰኔ 23 ቀን 1942 ዓ.ም. በቀድሞው ወሎ ጠቅላይ ግዛት ደሴ ከተማ የተወለዱት ዶ/ር ገሠሠ፣ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በደሴ ንጉሥ ሚካኤልና ወ/ሮ ስህን ሚካኤል ትምህርት ቤቶች የተከታተሉ ሲሆን፣ የ12ኛ ክፍልን በአዲስ አበባ ልዑል በዕደ ማርያም ትምህርት ቤት አጠናቀዋል፡፡በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በእንግሊዝኛ ዲፕሎማና የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ሲያገኙ በተመሳሳይ የማስትሬት ዲግሪያቸውን ከማንቸስተር ዩኒቨርሲቲ፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባና ከለንደን ዩኒቨርሲቲዎች በጣምራ አግኝተዋል፡፡ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ልዩ ልዩ ጥናቶችን ያደረጉ ሲሆን ሥራዎቻቸውንም ለኅትመት አብቅተዋል፡፡ዶ/ር ገሠሠ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነበሩ፡፡  ", "passage_id": "31bfc767f52ba2379531f14b2618b29e" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የደራሲ አዘጋጅና ተዋናይት ባዩሽ አለማየሁ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ።የአርቲስት ባዩሽ የቀብር ሰነ ስርዓት ወዳጅ ፣ ዘመዶቿ እና አርቲስቶች እንዲሁም አድናቂዎቿ በተገኙበት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።አርቲስቷ ባገጠማት ህመም ምክንያት በህክምና ስትረዳ ቆይታ ትናትና አመሻሻ ላይ ሕይወቷ ማለፉ የሚታወስ ነው፡፡ባዩሽ አለማየሁ በሃገር ፍቅር ቴአትር ቤት በተዋናይትነት ለረጅም አመታት አገልግላለች።በርካታ አጫጭር ተከታታይ ድራማዎችን፣ የመድረክ ትያትሮች ላይም በተዋናይነት እንዲሁም በአዘጋጅነት ስትሰራ ቆይታለች፡፡ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ለቤተሰቦቿ፣ለወዳጅ ዘመዶቿ እንዲሁም ለአድናቂዎቿ መፅናናትን ይመኛል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳየፋና ድረ ቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን! ", "passage_id": "d113606d69434f28d14ddf1e2b5cef4f" } ]
ff3bf79769db4909a3e5201697ac27e1
5b1f1ae27bf93604bf31d4cb3ecd3e3b
ተመራቂዎች የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት በማረጋገጥ የህዝብ አገልጋይ መሆን እንዳለባቸው ተገለጸ
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ተመራቂ ተማሪዎች የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት በማረጋገጥ የህዝብ አገልጋይ መሆን እንደሚገባቸው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር  ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ ገለጹ። የመቐለ የኒቨርሲቲ ለ28ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን ከ3 ሺህ በላይ ተማሪዎቹን ትናንት ማስመረቁን ኢዜአ ዘግቧል። በምርቃ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ፤ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን ትምህርት ቀጥለውና የተለያዩ ችግሮችን አልፈው ለምረቃ በመብቃታችሁ ‘እንኳን ደስ ያላችሁ’ መልዕክት ለተመራቂዎች ያሲተላለፉ ሲሆን፤ ተመራቂዎች ለአገራቸው ሰላምና ልማት በመሥራት ህዝባቸውን ማገልገል እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ተመራቂዎቹ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያካበቱትን እውቀት ሕዝባቸውን ለማገልገል እንዲጠቀሙበት ያስገነዘቡት ዶክተር ሙሉ፤ በክልሉ በተካሄደው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተማሪዎች ጉዳት እንዳይደርስባቸው ላደረጉት አስተዋጽኦም ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጎን በመሆን የከተማዋን ልማት እንዲያረጋግጡም ጠይቀዋል።ተመራቂ ተማሪዎች በበኩላቸው፤ በውጣ ውረዶች ውስጥ አልፈው ለዚህ በመብቃታቸው መደሰታቸውን የገለጹ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላም ያገኙትን እውቀት ተጠቅመው በቅንነትና በተታሪነት አገራቸውን ለማገልገል መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በዕለቱ ከተመረቁ ተማሪዎች አንድ የሦስተኛ ዲግሪ ተመራቂ ሲሆን፤ የተቀሩት የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች ናቸው። ከተመራቂዎቹ መካከልም 38 በመቶዎቹ ሴቶች ናቸው። ዩኒቨርሲቲውም በሁሉም የትምህርት መርሐ ግብሮች ከ30 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ እንደሚገኝም ታውቋል።በምርቃ መርሓ ግብሩ ላይ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የቦርድ አባላት መታደማቸውን ነው ኢዜአ የዘገበው።አዲስ ዘመን ታህሳስ9/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37587
[ { "passage": "ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከመላው አገሪቱ የተውጣጡ ከ3 ሺህ 696 መምህራን ጋር እየተወያዩ ነው፡፡ከመምህራን ጋር ቀጣይነት ያለውን ውይይት ማድረግ የመጪውን ትውልድ የመገንባት በተለይም አዲሱን የትምህርት ፍኖተ ካርታ ለመተግበር ቁልፍ ሚና እንዳለው ተገልጿል፡፡መጪው ትውልድ አገሩን ለማገልገል እንዲተጋ ማስቻልና ማሳወቅ መምህራን ለአገር ግንባታ የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ተናግረዋል፡፡በተጨማሪም መምህራን ዋርካ ናቸው በማለት ያለባቸውን የከለላ ኃላፊነት አውስተዋል፡፡ (ምንጭ፡-የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት)", "passage_id": "881c3aace37c91472a60631c3c32bfd0" }, { "passage": "በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተረጋጋና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር ሁሉም የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንዳለበት የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ ሞኮንን አሳሰቡ።የትምህርት ሚኒስቴር በዘንድሮ ዓመት ሰላማዊ የመማር ማስተማርን ለማረጋገጥ የሚያስችል ውይይት ከሐይማኖት አባቶች፣ ከአገር ሽማግሎዎች፣ ከአባ ገዳዎችና ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።በዚህ ወቅት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ እንደገለጹት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማሪያ፣ የምርምር፣ የጥበብ መፈለጊያ፣ ያለፉ በጎ የታሪክ ምዕራፎችን ማስቀጠያና ስህተት የተደረገባቸውን ደግሞ እንዳይደገሙ ጥረት የሚደረግበት ቦታ ነው።የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስብዕናቸው የተመሰገኑና ለሌላው አርአያ መሆን ሲገባቸው የልዩነትና የብጥብጥ መለያ መሆን የለባቸውም ብለዋል።እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዝግጅት ጊዜ ተማሪዎችን ከመጥራታቸው በፊት ያላቸውን ዕድሎችና ተግዳሮቶች ለይተው ጥፋቶችን መግታት የሚችሉበትን፣ የህግ የበላይነት የሚከበርበትን፣ መብትና ግዴታውን የሚያውቅ ትውልድ ለመፍጠር መስራት ይኖርባቸዋል።ለዚህም ቤተሰብ፣ የሐይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ዩኒቨርስቲዎቹ የሚገኙባቸው አካባቢ ማህበረሰብ አባላት የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችና ከንቲባዎች የውስጥ አደረጃጀትን በማጠናከር ተማሪዎች ከሚማሩበት አካበቢ ኀብረተሰብ ጋር እንዲዋሀዱና የጋራ መስተጋብር እንዲኖራቸው የሚያስችሉ የተለያዩ የበጎ ፍቃድ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር እንደሚገባም አመልክተዋል።የተማሪዎች ምክንያታዊነትና የዴሞክራሲ ባህልን በማዳበር ለአገራዊ ለውጥ እንዲተጉ፣ እንዲወያዩና ስለ አገራቸው እንዲያውቁ የሚያስችል የእርስ በርስ የውይይትና የክርክር መድረኮችን ማዘጋጀት ተገቢ እንደሆነም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ ጠቁመዋል።የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኮሙዩኒኬሽን ግንኙነትን በማህበራዊ ሚዲያ በማጠናከር ተማሪዎች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ወቅቱን የጠበቀና ፈጣን የሆነ ምላሽ መረጃን መስጠት ተገቢ እንደሆነም ገልፀዋል።ይህም ቤተሰብ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ እምነት አሳድሮ ልጆቹን እንዲልክ ያስችለዋል ብለዋል።የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በበኩላቸው “የ2011 ዓመት በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ ያሉ ተጋላጭነትን በምን መልኩ እንዝጋና የባለድርሻ ሚና” በሚል ባቀረቡት የመወያያ ርዕስ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለብጥብጥ የሚዳርጉ ትናንሽ የሚመስሉ ጥያቄዎች ላይ መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።በተለይ ተቋማቱ የጥበቃ፣ የክሊኒክ፣ የምግብ ቤት፣ የመኝታ ቤት አገልግሎትን እንደዚሁም  የሬጅስትራር፣ የኮሌጅ አስተዳደርና የመዝናኛ ቤት ላይ ለሚነሱ ችግሮች ጥንቃቄ የተሞላበት አፋጣኝ ምላሽ መስጠት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።ተማሪዎች ስለ አገራቸው ነባራዊ ሁኔታ እንዲያውቁና እርስ በርስ እንዲተዋወቁ የመኝታ ቤት ምደባ አገራዊ መልክ ይዞ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።በቀጣይ በተቋማቱ የህግ የበላይነት እንዲከበር፣ በስነ ምግባር ጉድለት የሚባረሩ ተማሪዎች ሌላውን እንዳያውኩ፣ የውኃና የመብራት መቆራረጥ ችግር ለመቅረፍ ሁሉም ተቋማት አስቀድመው ዝግጅት እንዲያደርጉም አሳስበዋል።የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ባለፈው ዓመት በመማር ማስተማር ሂደት የታዩት ችግሮች እንዲቀረፉ መንግስት የህግ የበላይነትና ሰላም ላይ መስራት እንዳለበት ተናግረዋል።የጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ ተጠባበቂ ፕሬዝዳንት አቶ ኤሊያስ ዑመር እንዳሉት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሚከሰቱ ችግሮች ተማሪዎች የመፍትሄ አካል አድርጎ መንቀሳቀስ ተገቢ ነው።የወለጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ኤባ ሚጀና በበኩላቸው ጥቂት ተደራጅተው የውሸት ድረ-ገጽ ከፍተው የዩኒቨርስቲውን ገጽታ ለማበላሸት በሚንቀሳቀሱት ላይ መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ ጠይቀዋል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባት አባ ኤርሚያስ እንዳሉት በተማሪዎች አቀባበል ላይ የፍቅርና የአክብሮት አቀባበል በማድረግ ሁሉም ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል።ሼህ አቡዱቃድር የተባሉ የሀይማኖት አባት በበኩላቸው በብሔር የሚለያዩትን ትተን ተማሪዎች ወደ ተሳሳተ አካሄድ እንዳይሄዱ ከመንግስት ጋር ሆነን ኃላፊነታችንን መወጣት ይኖርብናል ብለዋል።አባ ገዳ ቃበቶ ኤደሞ በሰጡት አስተያየት ደግሞ ኢትዮጵያዊያን በሌሎች አገራት መብታቸው ተከብሮ በሚሰሩበትና በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ተማሪዎች በሁሉም የአገሪቱ ክፍል ተንቀሳቅሰው እንዲማሩ ማድረግ ይኖርብናል ሲሉ ነው ያሳሰቡት።ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙባቸው አካባቢዎች ያሉ ማህበረሰብ ከትምህርት ተቋማቱ ጋር በጋራ ተማሪዎች ተረጋግተው እንዲማሩና ቤተሰቦቻቸውም አምነው ልጆቻቸውን እንዲልኩ የሚያስችል ተግባር ማከናወን ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።በውይይቱ ላይ ከሁሉም ክልሎች የተወከሉ የሐይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎችና ባለ ድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።መንግስት ብቁ ዜጋ ለመፍጠር ለሰው ኃይል ልማት ከአጠቃላየ ዓመታዊ በጀቱ እስከ 25 በመቶ የሚሆን መድቦ እየሰራ ነው ተብሏል። (ኢዜአ)", "passage_id": "2b87450e9403059f1a92ac2d7fe2df8a" }, { "passage": "ከፍተኛ አመራሩ ህብረተሰቡን ጥያቄ ከመመለስ ባሻገር ለልማትና ለዴሞክራሲ እንዲነሳ ማድረግ እንዳለበት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አስገነዘቡ ።ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ለ471 ከፍተኛ አመራሮች ከአንድ ወር በላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ትናንት ሲጠናቀቅ ባደረጉት ንግግር፤ ስልጠናው ውጤታማነቱ የሚረጋገጠው የህዝቡን ጥያቄ ከመመለስ ባሻገር ህብረተሰቡን ለልማትና ለዴሞክራሲ እንዲነሳ በማድረግ መሆኑን አስገንዝበዋል ። በተለይ በጥልቅ ተሃድሶ የተለዩ ግቦችን እንዲሳኩ መረባረብ እንዳለባቸው አመልክተዋል ፡፡ በሥልጠናው የታዩት መልካም ስነ-ምግባሮች አመራር አባላቱ ወደ ስራ ገበታቸው ሲመለሱ በተመሳሳይ ተግባራዊ በማድረግ የላቀ አፈጻጸም ማስመዝገብ እንዳለባቸውም አስረድተዋል።ስልጠናው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ በድርጅት ግንባታ፣ በአመራር ሳይንስ፣ በልማታዊ ኮሙኒኬሽን፣ በሁለተኛው የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ እንዲሁም በታላቁ መለስ ዜናዊ አስተምህሮ ላይና በሌሎችም ርእሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እእንደነበር ነው የተመለከተው ።በተለይም በተሃድሶ ግምገማ ተለይተው ከሚሰራባቸው ተግባራት መካከል አንዱ በመሆኑ ልዩ ሥፍራ ሊሰጠው ይገባል። ይህንም በማድረግ የሁለተኛው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ ማሳካት እንደሚቻል ጠቁመው፤ ለዚህም ኢህአዴግ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።የሰልጣኞቹ ተወካይ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ዶክተር ታቦር ገብረመድህን እንደገለጹት ስልጠናው ህብረተሰቡን በላቀ ደረጃ ለማገልገል የሚያስችል አቅም የተገኘበት መሆኑን አስረድተዋል ። \"በተሃድሶ የተለዩትን ሥራዎችም ዳር ለማድረስ የሚያስችል የአመለካከት ጥራትና የተሻለ እውቀት እንድናገኝ ያስቻለ ሥልጠና ነው\" ብለዋል። በሥልጠናው የተገኙትን የአመለካከትና የእውቀት ግብዓት ወደ ተግባር በመቀየር \"የህብረተሰቡን እርካታ ለማረጋገጥ ርብርብ ለማድረግ ቃል ገብተናል\" ሲሉም አረጋግጠዋል።በስልጠናው ከዞን እስከ ክልልና ፌደራል የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች ናቸው የተሳተፉ ሲሆን፤ሰልጣኞቹ ያወጡት ባለ ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫም በንባብ ቀርቧል-(ኢዜአ)።", "passage_id": "6a19fe21ea39203bcc03f8ec773ebd2d" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ህዳር 7/ 2006 (ዋኢማ) – የተጀመረውን የህዳሴ ጉዞ ከግብ ለማድረስ የኢህአዴግ ሴቶችና ወጣቶች ሊጎች አባላት ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የኢህአዴግ ሊቀመንበርና ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ገለጹ፡፡የኢህአዴግ ሴቶችና ወጣቶች ሊጎች 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያምን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአገር ውስጥና የውጭ እንግዶች በተገኙበት ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሯል፡፡ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም እንዳሉት ሴቶችና ወጣቶች ሊጎች ከ75 ፐርሰንት በላይ የሚሆነውን የብረተሰብ ክፍል የሚወክሉ በመሆናቸው የተጀመረው የህዳሴ ጉዞ እንዲሳካ የማይተካ ሚና አላቸው፡፡  በመሆኑም  በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የሁለቱም ሊጎች አባለት በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ሥራዎች እንዲሁም በጸረ ኪራይ ሰብሳቢነት ትግል ውስጥ ግንባር ቀደም ተዋናይ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል፡፡የየሊጎቹ አባላት እንዲሁም መላው ወጣቶች በጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ግንባታ ላይ ሁነኛ ተሳታፊዎች በመሆን አገሪቱ ወደፊት ልታረጋግ ጠው ለምትፈልገው የበለፀገ ኢንዱስትሪያዊ አገራዊ ኢኮኖሚ ግንባታ እውን መሆን ከማንም በላይ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡የኢህአዴግ ሴቶችና ወጣቶች ሊግ አባላት በሥነ ምግባር አበለጸጉ፣ ከኪራይ ሰብሳቢነትና ፀረ-ዴሞክራሲ የፀዱ፣ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ሁሉ ለሌላው የህብረተሰብ ክፍል ዓርአያ ሊሆኑ እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ተናግረዋል፡፡  ሊጎቹ አገራዊ ሀላፊነታቸውን ለመወጣት ለሚያደርጉት ጥረት ኢህአዴግና በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካላት አስፈላጊውን ድጋም እንደሚያደረጉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘው ገልጸዋል፡፡    በጉባኤ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የሱዳን ብሄራዊ ኮንግረስ ፓርቲ፣ የደቡብ ሱዳን ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ፤ የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር፣ የደቡብ አፍሪካው ኤ ኤን ሲና የቻይናው ኮሚኒስት ፓርቲ የድጋፍ መግለጫቸውን በተወካዮቻቸው አማካይነት  አቅርበል፡፡“በመለስ አስተምህሮ የተደራጀ የሴቶችና የወጣቶች ተሳተፎና ተጠቃሚነት ለህዳሴያችን” በሚል መሪ ቃል ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ጉባኤ ላይ ከመላው አገሪቱ የተውጣጡ ወጣቶችና ሴቶች ተሳታፊ ናቸው፡፡ጉባኤው የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ሴቶችና ወጣቶች ሊግ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር  በመምረጥ የተለያዩ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡", "passage_id": "f78d0933fbfbcf994b94418d05f20c24" }, { "passage": "ዜጎችን በሙያ ብቃት በማገልገል የመንግሥት ሠራተኝነት ክብርና ኩራት መሆኑን በተግባር ማሳየት እንደሚገባ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ገለጸ። የሲቪል ሰርቪስ ቀን «ኮቪድ -19 ወረርሽኝን በመከላከል ላይ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ላሉ የሕዝብ አገልጋይ ሲቪል ሰርቫንቶች ክብርና ዕውቅና እንስጥ» በሚል መሪ ሀሳብ በዓለም ለ18ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ14ኛ ጊዜ ታስቦ ሲውል፤ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር በዛብህ ገብረየስ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ «የመንግሥት ሠራተኝነት ትልቅ ክብር አለው እየተባለ በተለምዶ የሚነገረውን በተግባር መለወጥ ወሳኝ የሆነበት ጊዜ ላይ ነን» ብለዋል። የዓለም ፈተና የሆነውን የኮሮና ወረርሽኝን ተቋቁሞ ሕዝብን ማገልገል በተግባር የሚገለጽ ወገንተኝነት መሆኑንም የገለጹት ኮሚሽነሩ፤ የመንግሥት ሠራተኛው ራሱን ከችግር አውጥቶ ሌላውን ማገልገል የሚችለው የአመለካከት ለውጥ ሲያመጣ መሆኑንም ተናግረዋል። ሠራተኛው በቅንነትና በታማኝነት መርህ ዜጎችን ማገልገል ከኩራት በላይ መሆኑን ሊገነዘብ ይገባል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ወትሮም ቢሆን ክፍተት ይታይበት የነበረው የመንግሥት ሠራተኞች የማስፈጸም አቅም ውስንነት በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የበለጠ ጫና ውስጥ እንዳይገባ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑንም ገልጸዋል። ኮሚሽነሩ ከወረርሽኙ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የቀደመው አገልግሎታቸው ላይ መስተጓጎል እንዳይፈጠር እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ጠቅሰው፤ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ትግል የመንግሥት አመራሮችና ሠራተኞች እየከፈሉት ያለውን መስዋዕትነት በማድነቅ ከወረርሽኙ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው የሥራ መስኮች ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች ክብርና ዕውቅና መስጠት ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል። የመንግሥት ሠራተኞች በነፃነት አስበው በገለልተኛነትና በሙያዊ ብቃት ኅብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነትና ለሚሰጡት አገልግሎት ዕውቅና ለመስጠት የዓለም ሲቪል ሰርቪስ ቀን እ.ኤ.አ ከ2003 ጀምሮ የሚከበር መሆኑ ይታወቃል። አዲስ ዘመን ሰኔ 17/2012", "passage_id": "daa4d42ea1700e21d0a0ba361611d32d" } ]
fb7fcc6879f6876d8ed117007ca8ff9a
25a7ee05033fdbfd1c8d04bbf32b126c
በትግራይ ከጁንታው ጋር ተሰልፎ የነበረው የኦነግ ሸኔ አባል
ኢያሱ መለሰፈይሳ ተካ ይባላል። የ22 ዓመት ወጣት ነው። ትውልድና ዕድገቱ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ግንደ በረት ከተማ ነው። ትምህርቱን ከስምንተኛ ክፍል አቋርጦ ሀገራችንን ነፃ እናውጣ እያለ በሚሰብከው ታደሰ ጆንሴ በሚባል ሰው አማካኝነት ለኦነግ ሸኔ ሠራዊትነት ተመልምሎ ጊንጪ አካባቢ ጭልሞ በምትባል ቦታ ከጥር 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከ26 ባልደረቦቹ ጋር ስልጠና እንደወሰደ ይናገራል። ከስልጠና በኋላም ሁሉም ወደ መጡበት አካባቢ እንዲመለሱና ስልክ ሲደወልላቸው የሚፈለጉበት ቦታ ድረስ እንዲመጡ ትዕዛዝ ተሰጣቸው። እንደተነገራቸውም፣ የሰሜን ዕዝ ሠራዊት ላይ ጥቃት ከመፈጸሙ አስቀድሞ ማንነቱን በማያውቀው ሰው አማካኝነት ስልክ ተደወለለት። በተባለው ቦታ ተሰባሰቡና ጉዟቸውን ወደ ትግራይ አደረጉ፤ በእግርም በተሽካርካሪም ከተጓዙ በኋላ ጨርጨር አካባቢ ከትግራይ ታጣቂዎች ጋር ተቀላቀሉ። ፈይሳ ተካ ስም ተቀየረለትና የትግል ስሙ ብሩክ ተካ ሆነ። ምግብና ትጥቅ ተሟላላቸው፤ በወር ከስድስት ሺህ እስከ ሰባት ሺህ ብር እንደሚከፈላቸውም ተነገሯቸው ስምሪት ተሰጠው፡፡ከጥቂት ቀናት በኋላ በሰሜን እዝ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲፈጽሙ ትዕዛዝ ተሰጥቷቸው እንደነበርና እርሱ ግን አለመሳተፉን ነው ፈይሳ የሚናገረው። በአመራሮች በኩልም የትግሉ ዓላማ ሀገሪቱን ነፃ ለማውጣት እንደሆነ ይነግሯቸው እንደነበርም ይገልጻል። ቃል የተገባላቸውን የወር ደመወዝ ሲጠይቁ ግን መንግሥት የኢኮኖሚ ምንጮችን ስለዘጋብን መክፈል አንችልም የሚል መልስ እንደተሰጣቸው ፈይሳ ይናገራል። በዚህ መሃል መከላከያ ሠራዊት ህግን የማስከበር ዕርምጃ ሲጀምር ፈይሳ እጁን በሰላማዊ መንገድ ሰጥቷል። በማያውቀው ነገር በሰዎች ተታሎ በጥፋት ዓላማ ውስጥ  መሳተፉ እንደጸጸተው ነው ፈይሳ የሚናገረው። እንደ ፈይሳ ሁሉ፣ በርካታ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ከጁንታው ጋር አብረው ተሠልፈው የነበረ ሲሆን፤ ብዙዎቹም እጃቸውን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት እየሰጡ ይገኛሉ። ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ፣ በሃገራቸው የቀረበላቸውን ጥሪ ተከትለው ወደሃር መከላከያ ሠራዊት ከተመለሱ በኋላ አካባቢውን ጎብኝተው በተመለሱ ማግስት በሰጡት መግለጫ፤ አንዳንድ የኦነግ ሸኔ አባላት ከህወሓት ጁንታ ቡድን ጋር መሰለፋቸውን መግለጻቸው የሚታወስ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ9/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37581
[ { "passage": "የቄለም ወለጋ ዞን የጸጥታና ህዝብ ደህንነት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ ታምሩ በበኩላቸው አምስት ሰዎች በመከላከያ ኃይል መገደላቸውን አረጋግጠዋል።\n\nነገር ግን እሳቸው እንደሚሉት የተገደሉት ሰዎች ንጹሃን ሳይሆኑ የታጠቁ ሃይሎች ናቸው ብለዋል።\n\n\"የመከላከያ ሰራዊት እርምጃ የወሰደው በንጹሃን ዜጎች ላይ ሳይሆን በታጠቁ እና በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ሽፍቶች ላይ ነው\" ብለዋል።\n\n•በኦነግ እና በመከላከያ ሠራዊት መካከል በምዕራብ ኦሮሚያ ግጭት እንደነበር ተነገረ\n\n•«ኦነግ ሀገር ለመገንጠል ነው የምሠራው ብሎ አያውቅም» ሽጉጥ ገለታ (ዶ/ር)\n\n•በምዕራብ ኦሮሚያ የኦነግ ጦር አዛዥ ስለወቅታዊው ሁኔታ ምን ይላል?\n\nየሽመላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ ዮሃንስ ወጋ ለቢቢሲ እንደገለፁት \"ማክሰኞ ጠዋት የመከላከያ ሰራዊት ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ ህዝቡ ላይ ተኩስ ከፍቶ ነበር\" ብለዋል።\n\nበዚህ መካከል አምስት አባወራዎችና ወጣቶች መገደላቸውን አቶ ዮሃንስ ይናገራሉ።\n\nከተገደሉት ሰዎች መካከል አንዱ የአካባቢው ወጣቶች (ቄሮ) ሃላፊ ነው ብለዋል።\n\nየደህንነታቸው ሁኔታ ስጋት ውስጥ መግባቱን የሚናገሩት አቶ ዮሃንስ ለስደት እንደተዳረጉ ገልፀው \"የአካባቢው ነዋሪ አስከሬን እንቅበር ብለው ቢጠይቁም ተከልክለዋል። የአካባቢው ማህበረሰብ ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለው\" ብለዋል።\n\nሌላኛው የሽመላ ቀበሌ ነዋሪ አቶ መሃመድ የቀበሌው ነዋሪዎች ኦነግን እየደገፋችሁ ነው በማለት ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል።\n\nየተገደሉት ሰዎችን የኦነግ ወታደራዊ ልብስ በማልበስ የኦነግ ወታደሮችን ገድለናል ማለታቸውንም አቶ መሃመድ ገልጸዋል።\n\nአቶ ሃብታሙ በበኩላቸው በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን የተገደሉትም ሆነ የታሰሩት ንጹሃን ዜጎች እንደሆኑ ተደርጎ የሚናፈሰው ወሬ መሰረተ ቢስ ነው ይላሉ።\n\nከቀድሞው የኦነግ ሰራዊት አባላት መካከል ጫካ የቀሩት ሽፍታ መሆናቸውን አቶ ሃብታሙ ይናገራሉ።\n\n \"ከኦነግ ሰራዊት የተነጠሉ ናቸው። ሌላ ስምም የላቸውም። ስማቸውም ከሽፍታ የተለየ ሊሆን አይችልም\" ብለዋል አቶ ሃብታሙ።\n\nኦነግ በቅርቡ በሰጠው መግለጫ በኃይል የታጠቀ ምንም አይነት ወታደር የለኝም ማለቱ የሚታወስ ሲሆን የታጠቀው ሰራዊትም በእኔ የሚመራ አይደለምም ማለቱ የሚታወስ ነው። \n\nበምዕራብ ኦሮሚያ ከሚንቀሳቀሰው የመንግሥት ወታደር ጋር በሚያጋጥሙ ግጭት ምክንያት የግለሰቦች ህይወት እንደሚቀጠፍ የሚወጡ ሪፖርቶች ያሳያሉ።\n\n ", "passage_id": "0d77f180f6454820f1b2b9e1917c7db2" }, { "passage": "የኦሮሚያ ኮሚሽነር አለማየሁ እጅጉ ኩምሳ\n\nበዚህም መግለጫ ላይ የፀጥታ ኃይሎችንና ግለሰቦችን በድብቅ ሲያስገድሉ የነበሩት \"አባ ቶርቤ\" (ባለሳምንት) የተሰኘው ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል። \n\n•በኦነግ እና በመከላከያ ሠራዊት መካከል በምዕራብ ኦሮሚያ ግጭት እንደነበር ተነገረ\n\nኮሚሽነሩ በአካባቢው ግጭቶቹን በማነሳሳት ኦነግ ሸኔን የወነጀሉ ሲሆን፤ 12ቱ ፖሊሶችም የተገደሉት በኦነግ ሼኔ እንደሆነም ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ ኦነግ ሸኔን በገንዘብ የረዱ ሰዎችም ምርመራ እንደተጀመረም ኮሚሽነሩ አስረድተዋል። \n\nኮሚሽነሩ ጨምረውም የኦነግ መሪ የሆኑትን አቶ ዳውድ ኢብሳ በስም ጠቅሰው ከመንግሥት ጋር አብረው ለመስራት የሰላም ስምምነት የፈረሙ ቢሆንም በአንፃሩ ለሰላም እየሰሩ እንዳልሆነ ገልፀዋል። \n\nበኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ የፀጥታ ኃይሎችንና ግለሰቦችን በድብቅ ሲያስገድሉ የነበሩት \"አባ ቶርቤ\" (ባለሳምንት) የተባለው ቡድን ተጠርጣሪዎቹ \"አባ ቶርቤ\" በሚል መጠሪያ በመደራጀት ሰላማዊ ዜጎችን፣ የመንግሥት ባለስልጣናት እና የፀጥታ ኃይሎችን ሲገድሉ እና ተጨማሪ ባለስልጣናትን ለመግደል ሲያሴሩ ተጠርጥረው እንደተያዙ ተገልጿል። \n\n•ኦነግ ከመንግሥት ጋር ያደረኩት ስምምነት አልተከበረም አለ\n\nኮሚሽነሩ በቁጥር ሁለት ሺህ ሰባ (2070) ኤኬ47 የጦር መሳሪያዎች በቄለም ወለጋና ምዕራብ ወለጋ ዞን ከሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎችና ከባንክ ሦስት ሚሊዮን ብር እንደተዘረፈ ገልፀዋል። \n\n ", "passage_id": "77cdbb17fef534a3a747cd7bc4e06007" }, { "passage": "አቶ ዳውድ ጉለሌ በሚገኘው የኦነግ ጽህፈት ቤት ውስጥ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ''እየተጣሰ ነው'' ያሉት ከመንግሥት ጋር የደረሱት ስምምነት ምን እንደነበረ ዘርዝረዋል። \n\nበዚህ መሰረትም የተኩስ አቁም ስምምነቱ መከበር ፣ የመንግሥት የጸጥታ ኃይል አስከባሪ እና ደህንነት አካል ገለልተኛ እንዲሆን ማድረግ፣ የኦነግ ሠራዊት ወደ መንግሥት ኃይል እንዲካተት ማድረግ ከኦነግ ሠራዊት አንፃር ከመንግሥት ጋር የተስማሙባቸው እንደሆኑ አመልክተዋል።\n\nበተጨማሪም ባለፉት 27 ዓመታት የገቡበት ያልታወቁ የኦሮሞ ልጆች መጨረሻቸው ምን እንደሆነ መንግሥት ለህዝቡ እንዲያሳውቅ፣ ባለፉት 27 ዓመታት ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች ለሕግ እንዲቀርቡ ማድረግና ለውጡ ሁሉን አቀፍ እንዲሆን በሚሉ ነጥቦች ላይ ከስምምነት ላይ ደርሰው እንደነበር ተናግረዋል። \n\n• \"በኢትዮጵያ ፖለቲካ የኦነግ ስም ቅመም ነው\" የኦነግ የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ \n\n• «ኦነግ ሀገር ለመገንጠል ነው የምሠራው ብሎ አያውቅም» ሽጉጥ ገለታ (ዶ/ር)\n\n• “ትጥቅ መፍታት ለድርድር አይቀርብም”፡ መንግሥት\n\nነገር ግን የተጠቀሱት የስምምነት ነጥቦች ተግባራዊ እንዳልሆኑና እየተጣሱ መሆናቸውን ገልጸው፤ በምሳሌነትም ለተሃድሶ ስልጠና አርዳይታ ገብተው የቆዩ የድርጅቱ ወታደሮች አያያዝን አንስተዋል። \n\nበስምምነቱ መሰረት 1300 የሚሆኑ የኦነግ ወታደሮች ስልጠና ወስደው የመንግሥት የጸጥታ አስከባሪ አካልን እንዲቀላሉ ወደ ማስልጠኛ እንዲገቡ መደረጋቸውን ተናግረዋል።\n\n\"ይሁን እንጂ የኦነግ አመራሮች የሠራዊት አባላቱን እንዳይጎበኙ ተከልክለዋል፣ አንድ ፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም እንዲሰለጥኑ ይደረጋሉ፣ በካምፑ ውስጥ የጦሩ አያያዝ እንደ እስረኛ እንጂ ሰልጣኝ አይደለም\" በማለት ከስምምነት ያፈነገጡ ተግባራት እየተፈጸሙ እንደሆነ ተናግረዋል። \n\nከዚህ በተጨማሪ አቶ ዳውድ የኦነግ አባላት በአዲስ አበባ ከተማ በደህንነቶች እየታፈኑ እየተወሰዱ ነው ብለዋል።\n\nከዚህ ቀደምም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ አመራሮችን በመግደል ለግጭት መንስዔ የሆነው ኦነግ ነው ተብሎ የስም ማጥፋት እንደተፈፀመበት አመልክተው ክሱ ከእውነት የራቀ ነው ብለዋል። \n\n• \"ገዳ የወደፊቱ የፖለቲካ ስርዓት መሆን ይችላል\" ፕሮፌሰር አስመሮም ለገሰ \n\n ", "passage_id": "a11129d373a1eef73fa868723d724230" }, { "passage": "የሰሜን ዕዝን በ45 ደቂቃ ውስጥ መብረቃዊ ጥቃት በመፈጸም ከጥቅም ውጭ አድርገነዋል ብሎ የገለፀው የጁንታው አፈቀላጤ ሴኩቱሬ ጌታቸውን ጨምሮ 4 ከፍተኛ የጁንታው ቡድን አመራሮች ከነአጃቢዎቻቸውና ጠባቂዎቻቸው ተደመሰሱ፤ ሌሎች 9 የጁንታው ከፍተኛ አመራሮችም በቁጥጥር ስር ውለዋል።የመከላከያ ሰራዊት ሃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ እንደገለፁት ሴኩቱሬ ጌታቸውና ዘርአይ አስገዶምን ጨምሮ በርካቶች ሲደመሰሱ ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ እና ዶክተር ሰለሞን ኪዳኔና ሌሎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።በዚህም መሰረት፣ከተደመሰሱት ውስጥ ሴኩቱሬ ጌታቸው ከዚህ ቀደም በጁንታው መገናኛ ብዙሃን በኩል ጁንታው የመከላከያ ሰራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ መብረቃዊ ጥቃት ፈፅሟል ብሎ ማረጋገጡ ይታወሳል።ከተደመሰሱት በተጨማሪም 9 የጁንታው ቁልፍ አባላት በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን እነሱም፣የህወሃት ጁንታ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር የዋሉት በጫካና ዋሻ ለዋሻ ሲንቀሳቀሱ በተደረገ ጠንካራ አሰሳ መሆኑንም ብርጋዴል ጀኔራሉ ገልጸዋል።የአገር መከላከያ ሰራዊት እነዚህ የጁንታው ቁልፍ የጥፋት ቡድን አባላት እንዲደመሰሱና በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ያላሰለሰ ድጋፍ ላደረገው መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋናውን አቅርቧል።ሰራዊቱ ወንጀለኞቹን አድኖ ለመያዝ ቃል በገባው መሰረት ግዳጁን እየተወጣ መሆኑን ገልፀዋል።የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት የጀመረውን ቀሪ የጁንታውን ርዝራዦችን አድኖ ለመያዝና በህግ ተጠያቂ ለማድረግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አረጋግጠዋል።ህዝቡ እያደረገ ያለውን ድጋፍና ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አስተላልፈዋል።", "passage_id": "fe49c2922562557394dcc00c5106e35e" }, { "passage": "የተለያዩ ቡድኖች በተለያዩ ጊዜያት ከኦሮሞ ውስጥ ጠማማውን በመጠቀም የኦሮሞም ህዝብ መከራ ለማራዘም መሞከራቸውንና አሁንም ቢሆን የህወሓት ኃይል ኦነግ ሸኔ ብለው የጠቀሱትን ኃይል በመጠቀም ዳግም ሙከራ እያደረገ ነው ሲሉ የኦሮምያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አቶ ሽመለስ አብዲሳ ገለፁ።ህወሓት በበኩሉ ሕዝብ ለሚጠይቃቸው ጥያቄዎች እገሌ ነው የላከህ ማለት አግባብ አይደለም ብሏል።።\n", "passage_id": "ecb4e806077b5a546a612de0f9582121" } ]
6dce761a06168208250bbe2283e04a3b
72203bd15176967a2ac738e6dbf89085
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሙስናን ለመዋጋት እየሠራ መሆኑን አስታወቀ
ፋንታነሽ ክንዴአዲስ አበባ፡- ሙስናን ለመዋጋት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አስታወቀ። 17ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንንም ትናንት አክብሯል። የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ ፍርድ ቤት ከፈጣሪ በታች ህግን ለማስከበር ትልቅ ስልጣን ያለው፤ ህገመንግሥቱን የማክበርና የማስከበር ኃላፊነት የተጣለበት አካል ነው። ሙስናን ለመዋጋትና ለመከላከል ጉልህ ሚና የሚጫወት እንደመሆኑም ሙስናን ለመዋጋት የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። እንደ ወ/ሮ አሸነፈች ገለጻ፤ ሌሎች ህግን እንዲያከብሩ ለማድረግ በመጀመሪያ በተቋሙ ውስጥ ያሉ ሠራተኞች ህግን እንዲያከብሩ ማድረግ ይጠበቃል። ዳኞች የሚሰጧቸው ትክክለኛ ውሳኔዎች ሌሎች ሙስናንና ህገወጥነትን እንዲከላከሉና ህግን እንዲያከብሩ ያግዛሉ። ሌሎች የተቋሙ ሠራተኞች የሚሰጡት የተቀላጠፈ አገልግሎትም ህገ ወጥነትን ለመከላከልና ሙስናን ለመዋጋት የማይተካ ሚና አለው። የዳኝነት አካሉ በሰው ሕይወት፣ ሀብትና ንብረት እንዲሁም ነፃነት ላይ ውሳኔ የሚሰጥና ትልቅ ኃላፊነት ያለበት አካል መሆኑን የጠቀሱት ወ/ሮ አሸነፈች፤ ሙስናን እና በአጠቃላይም ህገ ወጥነትን ከመከላከል አንጻር ትልቅ ኃላፊነት እንዳለበት ተናግረዋል። ይህንን ለማረጋገጥ ዳኞች ስነ-ምግባርን በጠበቀ መልኩ ለተገልጋዮች በእኩልነትና በገለልተኝነት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ተከታታይ ስልጠና ሲሰጥ መቆየቱን ገልጸዋል።የዳኞች መተዳደሪያ የስነ ምግባር ደንብ በመሻሻል ለመጽደቅ በሂደት ላይ መሆኑን ያስታወቁት ወ/ሮ አሸነፈች፤ የፌዴራል መጀመሪያ ፍ/ቤት የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና የሠራተኞች የስነ-ምግባር መተዳደሪያ ደንብም መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ከእነዚህ ተግባራት በተጓዳኝ የመንግሥት የሥራ ሰዓትን ካለማክበር አስከ ትልልቅ ጉቦ መቀበል ድረስ ችግር የተስተዋለባቸው ሠራተኞች ላይ ከሥራ እስከማሰናበት የሚደርስ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው መደረጉንም አብራርተዋል። እንደ ወ/ሮ አሸነፈች ማብራሪያ፤ ዕርምጃ ከተወሰደባቸው ባሻገር ከየምድብ ችሎቱ ሬጅስትራሮችና አስተባባሪዎች ጋር በመተባበር የስነ-ምግባር ችግር ያለባቸው 60 ሠራተኞች መለየታቸውንና ምን ዕርምጃ ይወሰድባቸው በሚለው ላይ በማኔጅመንት ደረጃ ውይይት እየተደረገበት ነው። የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በዓለም ለ17ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ16ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የፀረ-ሙስና ቀን ‹‹የትውልድ የሥነ-ምግባር ግንባታን በጠንካራ ዲሲፕሊን በመምራት ሌብነትና ብልሹ አሠራርን በመታገል የህዝብ አመኔታን ያተረፈ የዳኝነት ስርዓት እንገነባለን›› በሚል መሪ ቃል አክብሯል። በበዓሉ ላይ የመነሻ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና የሠራተኞች የስነ-ምግባር መተዳደሪያ ደንብ መጽሐፍ ምርቃትም ተከናውኗል። አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37589
[ { "passage": "እያደገ በመጣው የስነምግባር መጓደልና  የሙስና መስፋፋት  ከመንግስት በላይ ተጎጂው ህብረተሰቡ እንደመሆኑ ችግሩን በመከላከል ረገድም ህብረተሰቡ ግንባርቀደም መሆን እንደሚገባው ተገለጸ፡፡ የፌዴራል ሥነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን ትናንት በ2011 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸሙን ገምግሞ  የ2012 በጀት አመት እቅዱ ላይ ከመወያየት\nባሻገር  በኮሚሽኑ የማቋቋሚያ አዋጅ ረቂቅ ላይም ከህዝብ ክንፍ አካላት ጋርም መክሯል፡፡ በወቅቱ እንደተገለጸውም፤ አሁን ላይ እያደገ የመጣውን የስነምግባርና የሙስና ችግር ህብረተሰቡ  ከማንም በላይ ተጎጂ\nበመሆኑ  በመከላከል ሂደቱም\nከፀረ ሙስና ተቋማትን ጥረት  ሊግዝ ይገባል፡፡ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አየልኝ ሙሉዓለም እንደተናገሩት፤ ኮሚሽኑ በስነምግባር ግንባታና ሙስናን በመከላከል ሂደት በርካታ ተግባራት እያከናወነ  ቢሆንም  የስነምግባርና ሙስና ችግር ከመቀነስ ይልቅ እየተባባሰ መሄዱ በህብረተሰቡ ላይ የሚፈጥረው ጉዳት የከፋ ነው፡፡ ችግሩን በመከላከል ሂደቱ ደግሞ ኮሚሽኑ ብቻውን የሚወጣው ሳይሆን የሁሉንም ተሳትፎ የሚጠይቅ እንደመሆኑ፤ የችግሩ ዋና ተጎጂ ህዝብ የጸረ ሙስና ኮሚሽኖችን በማገዝ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል፡፡ እንደ ኮሚሽነር አየልኝ ገለጻ፤ የጸረ ሙስና  ትግል ስራ በአንድ ተቋም ብቻ የሚከናወን ሳይሆን ቅንጅትን የሚሻ፤ በአጭር ጊዜ ታቅዶ የሚሳካም ሳይሆን ሂደትን የሚፈልግ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ኪሚሽኑ የሚችለውን እየሰራ ቢሆንም በመንግስት ቸልተኝነትና በሌሎችም ምክንያቶች የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አልተቻለም፡፡  በሙስና ምክንያት  በቢሊዬኖች የሚቆጠር  የህዝብና የመንግስት  ባክኗል።  እንዲህ ያሉ ድርጊቶች ደግሞ  ህዝቡን የሚያማርር ብቻ ሳይሆን የሚጎዳ በመሆኑ ሁሉም ሊታገለው ይገባል። በቀጣይም የህዝቡን ተሳትፎ ማሳደግና ጥቆማ ሰጪዎችም ያለስጋት መረጃ ማድረስ የሚችሉበትን አሰራር በሕግ ማዕቀፍ እንዲደገፍ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል ሃላፊው፡፡ በዚህ ረገድ የተዘጋጁ የሕግ ማዕቀፎችና የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ ጸድቀው ወደስራ ከገቡና ኮሚሽኑም ጠንካራ የመፈጸም አቅም ከፈጠረ የተሻለ ስራ ለመስራትና የተወሰነ ርቀት ለመሄድ የሚያስችሉ ናቸው፡፡ በመሆኑም ህዝቡም የድርሻውን ሊወጣ፤ ባለድርሻዎችም ተቀናጅተው ሊሰሩ ያስፈልጋል፡፡ ኪሚሽኑም አጋዥ የሆኑ የክልልና ተዋረድ መዋቅሮቹን የማጠናከር፤ የህዝብ ክንፉን የማስተማርና አቅም የመገንባት ተግባራትን ያከናውናል ተብሏል በውይይቱ ላይ፡፡ ወንድወሰን ሽመልስ ", "passage_id": "3416e9f453ce6fd09703126721a4cb29" }, { "passage": "የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የፍትሕ ሚኒስቴርና የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ከሚያዝያ 20 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ለአንድ ሳምንት በሚያከብሩት የፍትሕ ሳምንት፣ የአምስት ዓመቱ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የፍትሕ አፈጻጸም እንደሚገመገም ተገለጸ፡፡‹‹ፍትሕና ሁለንተናዊ ዕድገት›› በሚል መሪ ቃል በሚከበረው የፍትሕ ሳምንት፣ በአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የፍትሕ አፈጻጸም ምን ይመስል እንደነበር፣ ከኅብረተሰቡ አንፃር ምን ውጤት እንደተመዘገበና ያልተፈጸሙ ተግባራት ምን ምን እንደሆኑ ግምገማ እንደሚደረግባቸው፣ የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ልዑል ካህሳይ ገልጸዋል፡፡ሚኒስትር ዴኤታው እንዳብራሩት፣ ለአምስተኛ ጊዜ የሚከበረው የፍትሕ ሳምንት ለሰላም፣ ለቀልጣፋና ፍትሐዊ ለሆነ ልማት መረጋገጥ፣ ሥር የሰደደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲገነባና የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል፡፡ለበዓሉ መከበር ዋናው ምክንያት ከ2002 ዓ.ም. በኋላ አጠቃላይ የፍትሕ ሥርዓቱ የተሟላ የለውጥ ትግበራ የተጀመረበት ጊዜ መሆኑና የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ የአምስት ዓመት ፕሮግራምም እየተጠናቀቀ በመሆኑ፣ የበዓሉ ዋና ተዋናይ የሆኑት ተቋማት፣ ተቀናጅተው ሲሠሩ የከረሙትን አፈጻጸም የሚገመገምበትና ውጤቱና ድክመቱ የሚለይበት መሆኑን አቶ ልዑል ተናግረዋል፡፡የለውጥ ሒደት የፍትሕ አካላቱ ለብቻቸው በተናጠል የሚያካሂዱት ሒደትና እንቅስቃሴ አለመሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ከኅብረተሰቡ ጋር በመሆን የሠራውንና አገልግሎቱንም ሕዝቡ እንዴት እያገኘ እንደሆነ ሐሳቡን የሚገልጽበት መድረክ መፍጠሪያም መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ኅብረተሰቡ የራሱ ድርሻ ምን እንደሆነ ለይቶ የሚያውቅበትና የፍትሕ አካላቱን ከመደገፍ አንፃር የበኩሉን ሚና እንዲጫወት ለማስቻል በዓሉ ወሳኝ መሆኑንም አክለዋል፡፡ ከኅብረተሰቡ ግብዓትና ትችትም መቀበል ጠቃሚ በመሆኑ፣ በዓሉ አገራዊ ባህሪ ይዞ በፌዴራል ብቻ ሳይሆን በክልልም እንደሚካሄድ አቶ ልዑል አስታውቀዋል፡፡በበዓሉ ላይ የፓናል ውይይቶች እንደሚካሄዱ፣ ኤግዚቢሽን መኖሩን፣ ጥሩና ምርጥ ተሞክሮዎች እንደሚቀርቡ፣ የእግር ጉዞ እንደሚደረግ፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና በርካታ ሕዝብ የሚሳተፍበት የፍትሕ ሳምንት እንደሚሆንም ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡   ", "passage_id": "bd58403e1aad5631f05a2573879838da" }, { "passage": "– የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የአሰራር ሥርዓት ለማስፈን በአስፈፃሚ ተቋማት ላይ የሚያደርገውን የክትትልና የቁጥጥር ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አፈ-ጉባዔ አባ ዱላ ገመዳ ገለጹ። አፈ-ጉባዔ አባ ዱላ በተለይ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት አስፈፃሚ ተቋማት የተጣለባቸውን ተግባርና ኃላፊነት በግልጽነትና በተጠያቂነት መንፈስ በብቃት እንዲወጡ ምክር ቤቱ የጀመረውን የክትትልና ቁጥጥር ሥራ ይበልጥ አጠናክሮ ይቀጥላል። አስፈፃሚ ተቋማት ምክር ቤቱ በሚያደርገው የክትትል፣ የቁጥጥርና የድጋፍ ሥራ በመታገዝ ከፍተኛ መሻሻሎች ማሳየት መጀመራቸውን ገልጸዋል። በምክር ቤቱ አራተኛ የምርጫ ዘመን ሦስተኛ ዓመት ከፍተኛ ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች በዋናነት የአስፈፃሚ ተቋማት አፈፃጸምን በቅርበት በከታተልና በመቆጣጠር መልካም አስተዳደር እንዲረጋገጥ ማድረግ ነው ብለዋል። የምክር ቤቱ የቁጥጥርና የክትትል የትኩረት አቅጣጫም መልካም አስተዳደርን ጨምሮ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ፣ በግዙፍ ፕሮጀክቶች አፈፃጸም እንዲሁም በፀረ-ሙስና ትግል ላይ እንደሆነም አፈ-ጉባዔው አምልክተዋል።የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብ ባልተወገደበት ሁኔታ ምልዓተ ሕዝቡ በሙሉ ኃይሉ ወደ ልማት እንዳይገባ በሚያደርጉ ጉዳዮች ላይም ምክር ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።  የክትትልና ቁጥጥሩ ዓላማም የተጀመረውን አገራዊ ልማት እንዲፋጠንና ከልማቱም ሕዝቡ ተቃሚ እንዲሆን ለማስቻል እንደሆነም አፈ-ጉባዔው ገልጸዋል። አስፈፃሚ ተቋማት ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሰራር በማስፈን የሕዝቡ የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚነት ማጎልበት እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል።አገሪቱ በአሁኑ ወቅት በፈጣን የዕድገት ጎዳና ከመሆኗ ጋር ተያይዞ በማያቋርጥ የለውጥ እንቅስቃሴ ያለው ኅብረተሰብ የሚፈልገው በቀናት ሳይሆን በሰዓታት ውስጥ ምላሽ መስጠት የሚችሉ አስፈፃሚ ተቋማትን ነው። እናም ይህን የሕዝብ ፍላጎት የሚያረካ መልካም አስተዳደር ማስፈን የተቋማቱ ቁፍል ተግባር ሊሆን ይገባል፤ በዚህ በኩል ምክር ቤቱ ክትትልና ቁጥጥሩ ጠበቅ ያለ እንደሚሆን ጠቁመዋል። መልካም አስተዳደር የበርካታ ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው ያሉት አፉ-ጉባዔው ኅብረተሰቡ በቅንነት ከማገልገል ጀምሮ የልማትን ተጠቃሚነት እስከማረጋገጥ የሚደርስ ሰፊ መሰረተ ሃሳብ በመሆኑ አፈፃጸሙን ምክር ቤቱ በቅርበት እንደሚከታተል አስረድተዋል።በዚህ ረገድ ምክር ቤቱ ባሉት ቋሚ ኮሚቴዎች አማካይነት በሪፖርት፣ በመስክ ምልከታና የሕዝብ መድረክ በመፍጠር ከወትሮው በተለየ መልኩ የተጠናከረ የክትትልና የቁጥጥር ሥራ ማካሄዱን ይቀጥልበታል ብለዋል። የዚህ ሁሉ ማጠንጠኛ የፖለቲካ ኢኮኖሚውን በመለወጥ መካከለኛ ገቢ ያላት ኢትዮጵያን መፍጠር በመሆኑ ይህን ግብ ለማሳካት ግልጽነትና ተጠያቂነት የማስፈን ጉዳይ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል። ምክር ቤቱ የመልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ መሰረታዊ መርሆ የሆኑትን ግልጽነትና ተጠያቂነት በሚያረጋግጥ መልኩ የክትትልና ቁጥጥር ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለፃቸው ኢዜአ ዘግቧል።  የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 16 ቋሚ ኮሚቴዎች ያሉት ሲሆን በኮሚቴዎቹ አማካይነት የመንግሥት ተቋማት አፈፃፀምን ቁጥጥጥረና ክትትል ያደርጋል።", "passage_id": "2e4e0d40df0bd49936308b054722265b" }, { "passage": "አምስቱ የፍትሕ ተቋማት የሚባሉት የፌዴራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሚያገናኟቸው የሥራ ዘርፎች ላይ ውጤታማ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን አስታወቁ፡፡የተቋማቱ የሥራ ኃላፊዎችና ተወካዮች ዓርብ ሚያዝያ 12 ቀን 2010 ዓ.ም. በጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ እያንዳንዱ ተቋም በሕግ የተቋቋመበት ዓላማና ተልዕኮ አለው፡፡ በመሆኑም አንዱ ተቋም በሌላኛው ተቋም ሥራና ውሳኔ ላይ እንደማይገባ፣ ነገር ግን የተቋማቱ ዋና ዓላማ ፍትሕ ማስፈን በመሆኑ በአንድም ሆነ በሌላ የሚያገናኟቸው ሥራዎች እንዳሉ፣ ዓቃቤ ሕግ ከፖሊስ ጋር ሆኖ የተጠርጣሪዎችን ምርመራ እንደሚያደርግ፣ ተጠርጣሪው በፍጥነት እንዲለቀቅ ወይም በቀረበበት ማስረጃ መሠረት ሳይጓተት ክስ እንዲመሠርትበት፣ ፍርድ ቤትም የተፋጠነ ፍርድ በመስጠት ሳይዘገይ የክስ ሒደቱ እንዲካሄድ እንደሚያደርግም አስረድተዋል፡፡ ሌሎቹም ተቋማት በተመሳሳይ ሁኔታ ከታራሚ ጋር የተገናኙ ችግሮች ካሉ በመነጋገርና በመመካከር መፍትሔ እንደሚሰጥ አስረድተዋል፡፡የተቋማቱ ኃላፊዎች የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ዳኜ መላኩ፣ የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ተወካይ አቶ ማዕረጉ አሰፋ፣ የፌዴራል ፖሊስ ተወካይ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል ቀነዓ ያደታ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ይህደጎ ሥዩምና የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ተወካይ ዋና ሱፐርኢንቴንደንት አስቻለው መኮንን ሲሆኑ፣ መግለጫውን የሰጡት ከሚያዝያ 29 ቀን እስከ ግንቦት 5 ቀን 2010 ዓ.ም. ድረስ የሚከበረውን ስምንተኛው የፍትሕ ሳምንትን ምክንያት በማድረግ ነው፡፡ ‹‹ጠንካራ የፍትሕ ተቋማት ለአስተማማኝ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ›› በሚል መሪ ቃል፣ ለስምንተኛ ጊዜ የሚከበረው የፍትሕ ሳምንት፣ በአገር አቀፍ ደረጃ እንደሚከበር አስታውቀዋል፡፡ የተቋማቱ መሪዎችና ተወካዮች እንደተናገሩት፣ የፍትሕ ሳምንቱ በፌዴራል ደረጃ የሚከበረው በከተማ፣ በክፍለ ከተማና በወረዳ ደረጃ መሆኑን አስረድተው፣ በየደረጃው በሚከረበው ሥርዓት ላይ ኅብረተሰቡ ባለፈው ዓመት ላቀረባቸው ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚሰጥ፣ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎች እንደሚቀርቡና በድጋሚ ኅብረተሰቡ ለሚያነሳቸው ጥያቄ በግንባር ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በሰባተኛው ዙር ከኅብረተሰቡ ተነስተው የነበሩ የፍትሕ ማጣትና የተዛባ ፍርድና ረዘም ያለ ቀጠሮ ስለመስጠት፣ ያለምንም ጥፋት ታስሮ ስለመክረምና ከሌሎች ጥያቄዎችም የተገኘው ውጤት ምን እንደሆነ በጋዜጠኞች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ኃላፊዎቹ ምላሽ መስጠት አልቻሉም፡፡ በጥቅሉ በከተማ ደረጃ ከሕዝቡ ጋር ፊት ለፊት ሲገናኙ የተገኙ ውጤቶችን በሪፖርት መልክ እንደሚያቀርቡ ገልጸው፣ ውጤቶቹን ለጋዜጠኞች ለመንገር ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ በተጨማሪም ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ ከተደረገባቸውና ክስ ከተመሠረተባቸው በኋላ ወደ ማረሚያ ቤት ተልከው በአግባቡ መጠበቅና ክሳቸውን መከታተል ሲገባቸው፣ በማረሚያ ቤት ሆነው ግርፋትና የተለያዩ አካላዊ ጉዳቶች እንደ ደረሱባቸው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ሳይቀር ማረጋገጡን በተመለከተ ለተቋማቱ ኃላፊዎች ተገልጾላቸው፣ በእነሱ በኩል የወሰዱት ዕርምጃ ምን እንደሆነ ማብራሪያ ተጠይቀው ነበር፡፡በሰጡት ምላሽ ግን ለምን ተከሰስኩ ማለት እንደማይቻል፣ ዓቃቤ ሕግም ያለ ማስረጃ ሊከስ እንደማይችልና ተከሳሽ የወንጀል ድርጊቱን እንዳልፈጸመ ተከራክሮና ማስረጃ አቅርቦ ነፃ መውጣት እንጂ፣ የፍትሕ ተቋማትን መዝለፍና ወዳልሆነ ነገር መሄድ እንደሌለበት ተናግረዋል፡፡ ዜጎች ለረዥም ጊዜ ታስረው ከከረሙ በኋላ በነፃ ሲሰናበቱ ካሳ ስለሚያገኙበት ሁኔታ የተጠየቁት ኃላፊዎች፣ በሌሎች አገሮች አሠራሩ ያለ ቢሆንም በኢትዮጵያ ግን ካሳ እንዲሰጥ የሚያዝ የሕግ ድንጋጌ አለመኖሩን ጠቁመዋል፡፡ ወደፊት በሚወጡት የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕጎች ዕድል ምናልባት የሚካተትበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል አስረድተዋል፡፡      ", "passage_id": "89ec5c4b13cd64c26f24f3bb12c62995" }, { "passage": "\nጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝየሙስና ወንጀል ተግባራት ጋር ተያይዞ መንግሥት እየወሰደ ያለው ዕርምጃ የዘገየ አለመሆኑንና የባለሥልጣን ከለላ ያላቸው አይነኩም የሚለውን አመለካከት እንደማይቀበሉት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አስታወቁ፡፡ መንግሥት ከአሁን በኋላ በአገሪቱ አለመረጋጋትን የሚያስከትሉ ክስተቶችን እንደማይታገስም አስጠንቅቀዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ይህንኑ የገለጹት ቅዳሜ ነሐሴ 13 ቀን 2009 ዓ.ም. በተካሄደው በሦስተኛው የመንግሥትና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡ በተለይ ከሙስና ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያ መንግሥት እየወሰደ ያለውን ዕርምጃ እንደሚገፋበት አመልክተዋል፡፡ ከእሳቸው ማብራሪያ ቀደም ብሎ ግን በኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አፈወርቅ የቀረበው ሪፖርት፣ የመንግሥት ዕርምጃ የዘገየ ነው የሚል አመለካከትን ያንፀባረቀ ነበር፡፡በአገሪቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ የመጣውን ሙስናንና እያስከተለ ያለውን አደጋ በአፋጣኝ መፍትሔ መስጠት እንደሚያፈልግ የገለጹት አቶ ሰለሞን፣ ሙስና በአገር ዕድገትና ልማት ላይ ከፍተኛ አደጋ የሚያስከትል ዋነኛ የሥነ ምግባር ችግር መገለጫ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ምንም እንኳን ሙስናን በመከላከል ረገድ በመንግሥት የተከናወኑ የተለያዩ ሥራዎች ቢኖሩም፣ ችግሩን በሚፈለገው መጠን ለመቀነስ ባለመቻሉ ሳቢያ ከፍተኛ መጠን ያለው የአገር ሀብት ለምዝበራና ለብክነት በማጋለጥ አሳሳቢነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል፤›› ብለዋል፡፡መንግሥት ሲያስፈልግ ዘግይቶ ሙሰኞችን የሚይዝበት ሳይፈልግ የሚተውበት የሚመስል አሠራር በመተው የግሉን ዘርፍ፣ የፓርላማ አባላትን፣ ሲቪክ ማኅበራትንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያካተተ ወጥነት ያለው አደረጃጀት በመፍጠር ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት አሠራር መፈጠር ይኖርበታል ብለዋል፡፡በመንግሥት የሚወሰዱ ዕርምጃዎች አጥፊዎችን በሕግ ከመቅጣት ባለፈ ለሌሎች አስተማሪ ሊሆን የሚገባው በመሆኑ፣ የሚወሰዱ ዕርምጃዎችን ውጤት ለሕዝብ በይፋ እንዲገለጽ ማድረግ እንደሚገባ፣ ዘግይቶ የሚሰጥ ውሳኔ ጊዜ በመግዛት የፍርድ መዛባትን ስለሚያስከትል እንዲህ ዓይነት ጉዳዮችን ብቻ የሚያይ ልዩ ችሎት እንዲቋቋም አቶ ሰለሞን ጠይቀዋል፡፡አቶ ሰለሞን በዘመቻ መልክ የሚካሄዱ የፀረ ሙስና ሥራዎች የአንድ ወቅት ከመሆናቸው ባለፈ፣ በአጥፊዎች ላይ የሚወሰነው ቅጣት በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ካደረሱት ጉዳት አንፃር ሲመዘን ተመጣጣኝ ባለመሆኑና ሌሎች አጥፊዎችን ከማስተማር ይልቅ የሚያበረታታ በመሆኑ፣ የተፈለገውን ውጤት ሊያመጣ አልቻለም ብሎ ምክር ቤታቸው እንደሚያምንም ተናግረዋል፡፡ ‹‹በተለይ በቅርቡ በመንግሥት የተወሰደውን ዕርምጃ የተመለከትን እንደሆነ ከዚች ደሃ አገር በቢሊዮኖች የሚቆጠር የሕዝብ ሀብት ያላግባብ ሲመዘበርና ሲባክን የበይ ተመልካች በሆነው ሕዝብም ሆነ መንግሥት በኩል፣ ይህ ሁሉ ሲሆን የት ነበርን የሚያስብል አግራሞትና ትዝብት የሚፈጥር ነው፤›› ብለዋል፡፡ከዚህ ሐሳብ ጋር የማይስማሙ መሆኑን ያመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በበኩላቸው፣ ‹‹አሁን በኋላ መንግሥት እንደ ድሮው ዓይነት አይሆንም፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹እንኳን ከመንግሥት ባለሥልጣን የተጠጋ አሁን የመንግሥት ባለሥልጣናት መያዣ መጨበጫ አጥተዋል፤›› በማለት የሰሞኑን ክስተት አንፀባርቀዋል፡፡ አንዱ ተቆርጦ ሌላው እንደማይቀር ተናግረው፣ ስለዚህ አሁን እከሌ የሚባል ባለሥልጣን አለኝና እሱን ተገን አድርጌ እንደፈለግኩ እኖራለሁ የሚል ሰው ካለ እጁን መሰብሰብ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ ከሙስናና ከሕገወጥ ተግባራት ጋር በተያያዘ እየተወሰደ ያለውን ዕርምጃ በተመለከተም፣ ቀጣዩ የመንግሥት ዕርምጃ በንግዱ ዘርፍ ላይ የሚያነጣጥር መሆኑን ለማስገንዘብ ‹‹የሚቀጥለው ጥናታችን ወደ ንግዱ እየገባ ነው፤›› ብለዋል፡፡ይህ ንግግራቸው በትክክል የሚፈጸምና የአገር ጉዳይ በመሆኑ የሚተገበር መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ ‹‹ይቺ አገር ሰላማዊ ካልሆነች የማናችንም መኖር ዋስትና የለውም፡፡ ከዚህ በፊት አንዳንድ የሚወሩ ነገሮች ነበሩ፡፡ እከሌ የሚባል ባለሥልጣን ዘንድ የተጠጋ ስለሆነ አይነካም፡፡ እስቲ እንደማይነካ እናያለን፡፡ እውነቴን ነው የማይነካ ሰው የለም፡፡ ምክንያቱም ከግለሰቦች አገር ይበልጣል፤›› ብለዋል፡፡‹‹ይህ ሲደረግ ግን ሕግና ሥርዓትን ተከትለን ነው፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በአንድ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ ትልቁ ምሰሶ የሕግ የበላይነትን ማስከበር እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡ የአገሪቱ ሕገ መንግሥትና ሕጎች በሚፈቅዱት መሠረት ብቻ ዕርምጃ እንደሚወሰድና eza News 1ዕርምጀጃዕር ማንም ቢሆን ራሱን የመከላከል መብት እንደሚኖረው አስገንዝበዋል፡፡የኪራይ ሰብሳቢነትና የሙስና ምንጭ የሆኑ አምስት ጉዳዮች መኖራቸውን መንግሥት ሲናገር እንደቆየ ያመለከቱት አቶ ኃይለ ማርያም፣ ‹‹ከእነዚህ ውስጥ አንደኛው መሬት ነው፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹ከመሬት ሊዝ ጋር የሚገናኝ ችግር አለ፡፡ ይኼ ችግር የሚያጋጥመን በትልልቅ ከተሞች ነው፡፡ ለምሳሌ የሪል ስቴት አልሚዎችን ማየት ይቻላል፡፡ የሪል ስቴት አልሚዎችን ነገሩ ወደ እስር ቤት የሚያስገባም ቢሆንም ግድ የለም እንታገሳቸውና የወሰድከውን ትርፍ መሬት መልስ ከመለስክ በኋላ የቦታውን ትክክለኛ ሊዝ ክፈል ብለን ከባለሀብቶቹ ጋር ተደራድረን እስር ቤቱን ላለማጣበብ ሙከራ አድርገናል፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡አሁን መንግሥት የወሰደው ዕርምጃ የዘገየ ነው የሚለው አቋም መንግሥትን በማንቋሸሽ ዕርምጃውን ለማስቀረት የሚደረግ ፕሮፓጋንዳ ነው ብለውታል፡፡ ‹‹ይህንን አመለካከት በግሌ የምቀበለው አይደለም፡፡ እቺ እሳት እየተቀጣጠለች ወዴት ትደርሳለች ብሎ ያሰበ ሁሉ እያንቋሸሸ ነው፤›› ያሉት አቶ ኃይለ ማርያም እሳቱ መድረሱ፣ መንግሥትም ጠንክሮ መቀጠሉ እንደማይቀር አመልክተዋል፡፡የሙስና ዕርምጃው የላይኛውን የሥልጣን አካል አልነካም እየተባለ የሚነገረውም ለማንቋሸሽና ለማኮላሸት የሚደረግ ሙከራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ‹‹የፕሮፖጋንዳው ምንጭ በአግባቡ ካልጠራ በስተቀር ሒደቱን ለማኮላሸት የሚደረግ ሽረባ ነው፤›› ብለዋል፡፡ የንግዱ ኅብረተሰብ በዚህ ላይ አንድም ጥቆማ ያለመስጠቱን እንደ ምሳሌ አቅርበዋል፡፡የንግድ ምክር ቤቱም ሆነ የዘርፍ ማኅበራቱ አንድ ጥቆማ ያለማምጣታቸውን የጠቆሙት አቶ ኃይለ ማርያም፣ እስካሁን የደረሱ ጥቆማዎች ከሕዝብ የመጡ እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡‹‹የንግድ ኅብረተሰቡ አንድም ጥቆማ ሳያደርግ ጉዳዩን መንግሥት ላይ ደፍድፋችሁ የፀረ ሙስና ትግል በዚህ ይሄዳል ብላችሁ ካሰባችሁ አያስኬዳችሁም፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹ከማንም በላይ ሌባ የምታውቁት እናንተ ናችሁ፡፡ ምንም የሌለው ሰው በአጭር ጊዜ ውስጥ የብዙ ሕንፃዎች ባለቤት ሲሆን የምታውቁት እናንተ ናችሁ፡፡ አብራችሁ የምትበሉ የምትጠጡ፣ በሠርጉም በድግሱም አብራችሁ የምትቆዩት እናንተ ስለሆናችሁ፣ እናንተ እኛን አከናንባችሁ መንግሥት ዘግይቶ እንዲህ አደረገ ማለት አትችሉም፤›› በማለት የንግድ ኅብረተሰቡ ሙሰኞችን በመጠቆም ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡የፀረ ሙስና ንቅናቄ ተብሎ በሚደረግ መድረክና ስብሰባ የንግድ ምክር ቤቱ አመራሮች መኖራቸውን በማስታወስ፣ አሁን ምንም እንደማያውቁ አድርገው ያቀረቡት  እንዳልሆነም አመልክተዋል፡፡ ‹‹የፀረ ሙስና ትግል ኅብረተሰባዊ ካልሆነ፣ የሕዝብ ንቅናቄ ያልተፈጠረበት ትግል ካልሆነ ውጤቱ የተኮላሸ ይሆናል፡፡ የምንጋፈጠው ኃይል ቀላል  አይደለም፡፡ የራሱ መስመርና ኃይል ካለው ጋር ነው የምንጋፈጠው፡፡ በዚህ ትግል የንግዱ ኅብረተሰብ በሙሉ ቀልብ ተሳታፊ ከሆነ ተስፋ ሰጪ ነው፡፡ ይህንን በጋራ ሆነን አጠናክረን ከቀጠልን ፍትሐዊ የንግድ ኢንቨስትመንት ይኖራል፤›› ሲሉም ከመወቃቀስ ይልቅ በትብብር ለመሥራት ጥሪ አድርገዋል፡፡በቅዳሜው ስብሰባ ላይ ከሙስና ጋር በተያያዘ የሕዝብ ሀብት እየተመዘበረ ለመሆኑ ለቀረበው አስተያየት ጉዳዩን ከቡና የኮንትሮባንድ ንግድ ጋር አያይዘው መልስ ሰጥተውበታል፡፡ ቡና በሕገወጥ መንገድ እንደሚወጣ በመናገር፣ ይህንን የሚያደርጉት በሕጋዊ መንገድ ቡና እያቀረቡ ያሉ ነጋዴዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ‹‹በኮንትሮባንድ  ቡና ከአገር የሚያስወጡት አንድ እግራቸውን በማዕከላዊ ገበያ ያደረጉ፣ ሌላውን እግራቸውን ደግሞ ሱዳን ያስቀመጡ ሰዎች ናቸው፤›› በማለት ሕገወጥ ንግዱ ሕጋዊ ፈቃድ ባላቸው የሚከናወን እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ በሁለት እግሮች ይንቀሳቀሳሉ ያሉዋቸውን፣ ‹‹እግራችሁ ሰብሰብ ይበል!›› በማለት ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል፡፡እንዲህ ያለው ጉዳይ መስተካከል እንዳለበት ያሳሰቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹ለዚህም አንድ ጠንካራ ፀረ ኮንትሮባንድ ቡድን አቋቁሜያለሁ፡፡ አከርካሪ ሰብረንም ቢሆን እናስተካክላለን፤›› በማለት በመንግሥት ሊወሰድ የታሰበውን ዕርምጃ ጠቆም አድርገዋል፡፡ ቀጣዩ ዕርምጃ በንግድ ላይ ነው የተባለውም ለዚህ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ ‹‹እነዚያ አጭበርባሪ ኮንትራክተሮች ንብረታቸው ታግዷል፡፡ ስንትና ስንት ዓመት የለፉበትን ንብረት በሌብነት ምክንያት እያጡት ነው፤›› ያሉት አቶ ኃይለ ማርያም፣ ተዘረፈ የተባለውን በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ለማስመለስ የሚያስችል በቂ ንብረት አለ ብለዋል፡፡ ‹‹የተዘረፈ የሕዝብ ንብረት ተዘርፎ አይቀርም፤›› የሚል ምላሽም ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ረገድ ሥጋት እንደሌለም ጠቁመዋል፡፡ከዚሁ ማብራሪያ ጎን ለጎንም ሰሞኑን ከሙስና ጋር ተያይዞ ተጠርጥረው ስለታሰሩ ግለሰቦችና ስለታገዱ ኩባንያዎች ታዘብን ያሉትን እንዲህ ገልጸው ነበር፡፡ ‹‹ንብረታቸው የታገደባቸው ኩባንያዎች ስም ሲጠራ ብዙ ሰው ቦሌ ነበር፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቶች ሲባል ወዲያው ራሱን የጠረጠረም ነበር፡፡ እኛ ያልደረስንበትም የደረስንበትም ነበር፡፡ የዱባይ አውሮፕላን ተጨናንቆ ነበር፤›› ብለዋል፡፡ እዚያ ከመድረስ በፊት መጠንቀቅ እንደሚያሻ ያመለከቱት አቶ ኃይለ ማርያም፣ ‹‹ያንን ሁሉ ለፍተው ያገኙትን ንብረት ጥለው ከመኮብል በፊት አርፎ መቀመጥ ይሻላል፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹በእርግጥ እነዚህ ሰዎች እዚያ (ዱባይ) ገንዘብና ንብረት እንዳላቸው ይታወቃል፡፡ ቢሆንም ዋናው ንብረት እዚህ ነው፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡ ‹‹የቡናውንም ቢሆን መልክ እናስይዛለን፡፡ ይኼ ካልሆነ አገራችን ችግር ውስጥ መውደቋ አይቀርም፡፡ ስለዚህ በዚህ ትግል ውስጥ በጋራ እንሳተፍ፡፡ ከቡና ጋር ተያይዞ አለ የሚባለውን ችግር ብናይ ጥሩ ነው፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡በዚህ የምክክር መድረክ አቶ ኃይለ ማርያም አፅኖት ሰጥተው ካስገነዘቡዋቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ በባህር ዳር አካባቢ ከንግዱ ኅብረተሰብ አባላት መታሰር ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ‹‹በባህር ዳር አካባቢ ከመረጋጋት ጋር ተያይዞ መንገራገጭ ቢኖርም ይህንን እናስቆመዋለን፤›› ብለዋል፡፡ በአማራ ክልል ታስረዋል የተባሉ ሰዎች ንፁኃን ናቸው የሚለውን አስተያየት አቶ ኃይለ ማርያም እንደማይቀበሉት ገልጸዋል፡፡ ‹‹የታሰሩት ሰዎች ተጠንተው የታሰሩ ናቸው፡፡ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ቀድሞም የነበሩ ሰዎች ናቸው፤›› ብለዋል፡፡‹‹ሰውዬው ስሙ ማንም ሊሆን ይችላል፡፡ የትኛውም ዓይነት ክብር ሊኖረው ይችላል፡፡ ወጣት፣ ታክሲ፣ ባጃጅ እየቀሰቀሰ፣ ገንዘብ እየሰጠ፣ ዝጉ እያለና እያሰማራ ሕፃናቱን ከፊት እንድናገኝ አናደርገውም፤›› በማለት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹አሁን ግን ሥሩን ፈትሸን እንነቅላለን፡፡ እስካሁንም ከወጣቶቻችን ጋር የተጋጨነው ይበቃናል፤›› በማለት ሲናገሩ ተሳታፊዎች የሞቀ ጭብጨባ ችረዋቸዋል፡፡በዚህ የምክክር መድረክ ላይ የተለያዩ ሐሳቦች የተሰነዘሩ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ከንግድ ማኅበረሰቡ ለተጠየቁ ጥያቄዎች ተጨማሪ ማብራሪያ ይሰጡ የነበሩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ በቅዳሜው ስብሰባ ምንም ዓይነት አስተያየት አልሰጡም፡፡", "passage_id": "6de39409cffc073c34ed5e58c6d761c4" } ]
2cb6149017366dc1b6ad8123c1101878
56b170014ca5f8e2f5eeaf91f0816422
በኮቪድ 19 ምክንያት በከፊል አቋርጦ የነበረው የህዝብ ቤተ መጽሐፍት ወደሥራ ሊመለስ መሆኑ ተገለጸ
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡- በኮቪድ-19 ምክንያት ለሥምንት ወራት አገልግሎቱን በከፊል አቋርጦ የነበረው የህዝብ ቤተ መፅሐፍት አገልግሎት ክፍት ሊደረግ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፅሐፍት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡በኤጀንሲው የህዝብ ቤተ መፅሐፍት ዳይሬከተር አቶ ያሬድ ተፈራ እንደገለጹት፤ የህዝብ ቤተ መፅሐፍቱ ኮቪድ-19 በኢትዮጵያ ከተከሰተበት መጋቢት ወር ጀምሮ ለሥምንት ወራት በስፋት አገልግሎት መስጠት ሳይችል ቆይቷል፡፡ አሁን ላይ ግን የኮሮና ቫይረስን በመከላከል የህዝብ ቤተ መፅሐፍቱ አገልግሎት መስጠት የሚችልበት መመሪያ በመዘጋጀቱ አገልግሎቱ ክፍት ይደረጋል፡፡እንደ አቶ ያሬድ ገለጻ፤ የህዝብ ቤተ መፅሐፍቱ ከዚህ በፊት ተመራማሪዎችና ቤተ መዛግብትን ለመጠቀም ለሚመጡ ተገልጋዮች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም ለብዙሃኑ ህዝብ ዝግ ሆኖ መቆየቱ ለተጠቃሚዎች ጫና ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ አሁን ላይ ከሕፃናት ውጪ ለሌሎች ተጠቃሚዎች ከፍት የሚሆንበት ሁኔታ እየተመቻቸ ሲሆን፤ መመሪያውም ተገልጋዮችም ሆኑ ሠራተኞች ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ሳይንስ ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚወጡ መመሪያዎችን በሚገባ ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡በኤጀንሲው የስልጠና እና የምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መኮነን ከፍያለው በበኩላቸው፤ የህዝብ ቤተ መፃሕፍቱ ለህዝብ ክፍት በሚሆንበት ወቅት መመሪያው በሚፈቅደው መሰረት በቤተ መፃሕፍቱ ውስጥ ያሉትን ወንበሮች በመቀነስ በአንድ ጠረንጴዛ ውስን ሰዎች እንዲገለገሉ የሚያስችል አሠራር ተዘርግቷል ብለዋል፡፡ በዚህም ከዚህ በፊት ከ1ሺ 200 በላይ ሰዎችን ያስተናግድ የነበረው ቤተ መፃሕፍት አሁን ላይ ኮሮናን ለመከላከል በሚያስችል መንገድ 326 ወንበሮች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ይህ የሆነውም የቤተ መፃሕፍቱ ወንበሮች ደንበኞች ከተገለገሉባቸው በኋል ከሦስት እስከ ሰባት ቀን ኳራንቲን በማድረግ አስፈላጊውን የኬሚካል ርጭት ተደርጎላቸው አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡የብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃሕፍት ኤጀንሲ ከዚህ በፊት ከ2፡30 እስከ 9 ሰዓት ይሰጥ የነበረው አገልግሎት በአሁኑ ሰዓት የ24 ሰዓት አገልግሎት ለመስጠጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁም ተገልጿል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ፣ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37597
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጣሊያን መንግስት ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ትምህርት ቤቶችን እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ሊዘጋ ነው።ትምህርት ቤቶቹ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በሚል እንደሚዘጉ የሃገሪቱን ባለስልጣናት ዋቢ ያደረገው የሬውተርስ ዘገባ ያመላክታል።ከዚህ ጋር ተያይዞም ለሁለት ሳምንታት ይዘጋሉ ነው የተባለው፤ አሁን ላይ የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ በሆነባቸው የሃገሪቱ ሰሜናዊ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል።በጣሊያን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ይገኛል።እስካሁን ባለው መረጃም 79 ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ፥ ከ2 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል።ምንጭ፦ ሬውተርስ ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!\nhttps://t.me/fanatelevision", "passage_id": "40164e0042f632671bd56cd9f6c0d4b5" }, { "passage": "በኢትዮጵያ የኮሮና ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ከ42 ሺሕ በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ይማሩ የነበሩ ከ26 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ተስተጓጉለው የቆዩ ቢሆንም፣ በ2013 ዓ.ም. ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ ጥናት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በኢትዮጵያ የኮሮና ወረርሽኝ ሥርጭት እየጨመረ ከፍተኛው መጠን ላይ ደርሶ እያሽቆለቆለ አለመሆኑና አሁን ያለው አብዛኛው የትምህርት ቤቶች አቋም ወረርሽኙን ተከላክሎ ለማስተማር አያመችም በማለት ጤና ባለሙያዎች በተለያዩ ጊዜያት ሥጋታቸውን ቢገልጹም፣ ትምህርት ሚኒስቴር የቫይረሱ ሥርጭት ያለበት ሁኔታ እየተገመገመ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ በደረጃ ለመክፈት የሚያስችሉ ሁኔታዎች እየተጤኑ መሆኑን ገልጿል፡፡በ2013 ዓ.ም. ትምህርት ለማስቀጠል በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ መግለጫ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ፣ ትምህርት ለማስጀመር የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ለመዳሰስ የጥናት ቡድን መቋቋሙን፣ በትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20 እስከ 25 ተማሪዎች ለማስተማር የሚያስችል አቅም ስለመኖሩ የመለየት ሥራ እየተካሄደ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ጥናቱ ተጠቃሎ ትምህርት የሚያስከፍት ሁኔታ ካለ የተማሪዎችን ርቀት ለማስጠቅ በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ እንዲቀመጥ እንደሚደረግ፣ በፈረቃ ትምህርት መስጠት፣ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መገንባትና የማኅበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ለማስተማሪያነት መጠቀም እንደ አማራጭ እንደሚውሉ ተነግሯል፡፡በትምህርት ቤቶች ውስጥ ውኃ እንዲኖር ማድረግ፣ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘርና የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ የማቅረብ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተገልጿል፡፡ ሚኒስትር ዴኤታው እንዳብራሩት፣ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ወላጆችም ሆነ ልጆች ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ በመሆኑም የትምህርት ቤቶች መከፈት ችግሩን ለማቃለል አንድ ደረጃ ብለው፣ ነገር ግን በኮሮና ወረርሽኝ ወቅት ትምህርት ቤቶች እንዲሁ እንደቀደመው እንደማይከፈቱ አስታውቀዋል፡፡ተማሪዎችን ከወረርሽኙ ለመከላከል ሲባል በዓለም ከአንድ ቢሊዮን በላይ ተማሪዎች ቤት እንዲዘጉ ተደርጓል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሕፃናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) እንደሚለው በዓለም በቫይረሱ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ ትምህርት ቤት ከዘጉ 134 አገሮች ውስጥ፣ 105 ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት ወስነዋል፡፡ ከ105 አገሮች 59 ያህሉ ትምህርት የከፈቱና ለመክፈት ያቀዱ ናቸው፡፡ምንም እንኳን ውሳኔ የሚያስተላልፉት መንግሥታት ቢሆኑም ጉዳቱና ጥቅሙ በጥልቅ መታየት እንዳለበት የሚያሳስበው ዩኒሴፍ፣ አገሮች እንደሚኖሩበት ነባራዊ ሁኔታ የማኅበረሰብ ጤና፣ ማኅበራዊና የኢኮኖሚ አንድምታዎችን ማየት ይኖርባቸዋል ይላል፡፡ትምህርት ቤቶች የሚከፈቱ ከሆነ የየአገሮች የማኅበረሰብ ጤና ምላሽ፣ ተማሪዎችን፣ ወላጆችን፣ መምህራንንና ሌሎች ሠራተኞችን የመከላከል አቅሙ አለው ወይ የሚለው ሊታይ እንደሚገባም ያሳስባል፡፡ ", "passage_id": "374e5d6a6b920248a55981ac9cb1c00d" }, { "passage": "በክረምቱ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ የሚገኙ ትምህር ቤቶችን መልሶ ለማደስ 150 ሚሊዮን ብር በጀት መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ በተለይም ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት በዘንድሮ የክረምት መርሃ ግብር በትምህርት ዘርፉ በርካታ ስራዎች የሚሰሩ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ በከተማዋ የሚገኙ ሁሉንም የመንግስት ትምህርት ቤቶች ማደስ ይገኝበታል። እንደ ምክትል ሃላፊው ገለፃ በዚሁ የክረምት መርሃግብር ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛና የመሰናዶ ትምህር ቤቶች ድረስ ያሉ 488 የከተማዋ ትምህርት ቤቶች ይታደሳሉ። ለዚሁ እድሳት ማከናወኛም ትምህርት ቢሮ 150 ሚሊዮን ብር በጀት በመያዝ ከከተማው የኮንስትራክሽን ቢሮ ጋር ስምምነት አድርጓል። በከተማው ኮንስትራክሽን ቢሮ በኩል በእድሳትና ጥገና፣ በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽን፣ በግቢ ማስዋብና የአጥር ስራ አራት ኮዶች ተከፋፍሏል ያሉት ምክትል ሃላፊው በነዚህ ኮዶች ውስጥ በተለቀቀው በጀት ስራዎች የሚከናወኑ ይሆናል። በአሁኑ ወቅትም የዋጋ ዝርዝር መግለጫ እየተሰራ ሲሆን ይህ እንዳለቀ በእያንዳንዱ ትምህርት የሚሰሩ ስራዎች ተለይተው ይከናወናሉ። በእድሳቱ ሂደት ትምህርት ቤቶቹን የማዘጋጀት፣ የሰው ሃይላቸውን የማንቀሳቀስ ተግባር የትምህት ቢሮ ስራ እንደሆነም ምክትል ሃላፊው ገልጸው፤ የተቋራጭነት የማማከርና የግንባታ አስተዳደርን በሚመለከት ደግም የከተማው ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊነት መውሰዱን ጠቁመዋል። በዚህ አጭር ግዜ ውስጥም ማጭበርበር የሌለበትና ጥራቱን የጠበቀ ስራ ለመስራት ታቅዷል የ2012 ዓም የትምህርት ዘመን ከመጀመሩ በፊትም የእድሳት ስራው ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ምክትል ሃላፊው ገልፀዋል። የአዲስ አበባ\nከተማ አስተዳደር በከተማዋ\nየሚገኙ የመንግስት ትምሀርት\nቤቶችን በራሱ አቅም\nእንደሚያድስ ከሳምንት በፊት\nየገለፀ ሲሆን በእድሳት\nሂደቱ የግል ባለሃብቶችና\nሌሎች ባለድርሻ አካላት\nእንዲሳተፉ የአሰራር ስርት\nበትምህርት ቢሮ በኩል\nመዘርጋቱ ታውቋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 10/2011 ", "passage_id": "76e7a1b2728ef8bb9b7ed1f689351b1a" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ኪሎ ሳይንስ ፋኩልቲ ከ100 ዓመታት በላይ ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ የተሰበሰቡ የእጽዋት እና እንስሳት ናሙናዎችን የያዘው የሙዚየም ህንጻ አደጋ ላይ እንደሚገኝ ባለሙያዎች ገለጹ። የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር በበኩሉ ጥናት አድርጎ በቅረቡ ህንጻውን ለማደስ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ፋኩልቲው ዲጂታላይዜሽን ባለሙያ አቶ ፍሰሃ ጌታቸው በበኩላቸው ህንጻው በአጼ ኃይለስላሴ ዘመን የተገነባ መሆኑን አስታውሰው በፍጥነት እድሳት  ካልተደረገለት ኢትዮጵያ ያሏትን ከ160ሺ በላይ የዕጽዋት ምርምር ሃብቶች ልታጣ እንደምትችል አስጠንቅቀዋል። ህንጻው ከማርጀቱ እና ከመሰነጣጠቁ ባሻገር ከ100 ዓመታት በላይ ያስቆጠሩ የሀገሪቱ ሀብቶች በጠባብ ቦታ ታጭቀው እንዲቀመጡ አስገድዷል። ሙዚየሙ የተጨናነቀ ከመሆኑ አንጻር ከዚህ ቀደም እሳት መፈጠሩን ያስታወሱት አቶ ፍሰሃ፣ሰዎች በወቅቱ በመኖራቸው በፍጥነት ባይጠፋ ኖሮ አደጋው በሙዚየሙ የሚገኙትን መተኪያ የሌላቸውን ሃብቶች የማውደም አቅም ነበረው ። በሌላ በኩል ባለሁለት ወለል ህንጻ የሆነው ሙዚየም የላይኛው ወለል ፈርሶ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሶ እንደሚያውቅ አስረድተዋል። በመሆኑም ለህንጻው አፋጣኝ እድሳት ከማከናወን ባሻገር በቋሚነት ዕጽዋቱን ጠብቆ ለምርምር ሥራ ማዋል እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ከውጭ አገራት እና አገር ውስጥ ባለሙያዎች የተሰበሰቡ የእጽዋት ዝርያዎች በሙዚየሙ መኖራቸውን የሚናገሩት አቶ ፍሰሃ፤ ከዚህ በተጨማሪ የእንስሳት አካላት ማሳያ ሙዚየም እና የተለያዩ ተፈላጊ የጥናት መጽሐፍት በህንጻው መኖራቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም የችግሩን ግዝፈት ተመልክቶ በአንድ ጀንበር በርካታ ሃብት ሊጠፋ የሚችልበትን አደጋ በማጤን የእጽዋት ናሙናዎቹን ከነሙሉ መረጃቸው ወደዲጅታል መረጃ ለመቀየር ጥረት ማድረግ ይገባል። በዋናነት ግን የህንጻ ግንባታ እና እድሳቱ አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነ በየጊዜው ጥያቄ ቢቀርብም ምላሽ አለመሰጠቱን አስረድተዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእጽዋት ባዮሎጂ እና ባዮዳይቨርሲቲ ማኔጅመንት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዶክተር ቢቂላ ወርቅነህ እንደገለጹት፣ በሳይንስ ፋኩልቲው በሚገኘው ሙዚየም ውስጥ ከ100 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያላቸው የእጽዋት ሃብቶች ለአደጋ ተጋልጠው ይገኛሉ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የግንባታ ፕሮጀክት ኃላፊ ኢንጂነር አርዓያ ተክለሃይማኖት ይህንኑ ጉዳይ አስመልክተው ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች በአራት ኪሎ ሳይንስ ፋኩልቲ የሚገኘውን የሙዚየም ህንጻ እርጅና በአግባቡ እንደሚያውቁ ተናግረዋል። ሙዚየሙ በያዛቸው የሀገር ሃብቶች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ በማሰብ ለህንጻው ጥገና ለማከናወን ጥናቶች እየተደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ለህንጻው እድሳት ምን ያህል ወጪ እንደተመደበ እንደማያውቁ የተናገሩት ኢንጂነር አርዓያ፣ የብሩ መጠን ከጥናቱ በኋላ የሚታወቅ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው፣የሙዚየሙን መጨናነቅ ለመቀነስ የማስፋፊያ ግንባታ ከዩኒቨርሲቲው አቅም ጋር ታይቶ ወደፊት ምላሽ የሚሰጠው ቢሆንም በ2012 ዓ.ም ግን ሙዚየሙን ወደማደስ ሥራ ይገባል። በመሆኑም በውስጡ የያዛቸውን ንብረቶች በማይጎዳ መልኩ ደረጃ በደረጃ ክፍሎቹን እያደሱ ጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።አዲስ ዘመን ቅዳሜ ጳጉሜ 2/2011ጌትነት ተስፋማርያም ", "passage_id": "2bf9c4e0c62058f0e61f3a2c2bcda353" }, { "passage": "እነሆ ምሳሌ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት ኤጀንሲ ዓይነሥውራንን ተደራሽ ለማድረግ መጻሕፍትን በድምጽ ቀርጾ ስለማስፋፋት ከጋዜጠኞች፣ ከተራኪ አርቲስቶችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር አንድ የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ውይይቱም ባለፈው ማክሰኞ ታህሳስ 16 ቀን በኔክሰስ ሆቴል የተደረገ ነው፡፡ ይህንን ሁነት በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የሚተላለፈው ብራና የተባለው የሬዲዮ ፕሮግራም ጥቆማ ይሰጣል፡፡ ይህን ፕሮግራም ሰምቶ ነበር ወጣት አቤል አያሌው ውይይቱ ወዳለበት ቦታ የሄደው፡፡አቤል ዓይነ ሥውር ነው፤ ለዚህም ሬዲዮ ባለውለታው እንደሆነ ይናገራል፡፡ ይህንን የውይይት መድረክ እንኳን የሰማው በሬዲዮ ነውና፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ሁኔታ ለዓይነ ሥውራን ምቹ ሁኔታ የለም፡፡ መጻሕፍት በድምጽ ተቀርጸው አይቀመጡም፡፡ ለዚህም በአሜሪካን አገር ኮሎሮዶ ግዛት ያለውን ተሞክሮ እንደ ምሳሌ ያነሳል፡፡ በኮሎሮዶ ‹‹ናሽናል ፌዴሬሽን ኦፍ ዘ ብላይንድ›› የተባለ ድርጅት በፌዴሬሽን ደረጃ ተቋቁሞ ነው የሚሰራው፡፡ ይህ ፌዴሬሽን ለአይነ ሥውራን መደረግ ያለበት ነገር ሁሉ እንዲደረግ ይከታተላል፡፡በኢትዮጵያ ውስጥ ግን ብዙ የአካል ጉዳተኛ እያለ የዚህ አይነት አሰራር የለም፡፡ በመሆኑም እንዲህ አይነት ተሞክሮ ካላቸው አገራት ልምድ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ያሳስባል፡፡የውይይቱ ተሳታፊ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ካሱ ደግሞ ሌላ ሀሳብ ያነሳሉ፡፡ የድምጽ ቤተ መጻሕፍት በተለያዩ የዓለም አገራት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት የሚሰራበት ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ግን ቤተ መጻሕፍት ማለት መጽሐፍ ብቻ ያለበት ማለት ነው፡፡ ይሄ ደግሞ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አይሄድም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተጻፈው ይልቅ ያልተጻፈው የስነ ጽሑፍ ሀብት ይበልጣል፡፡ ስነ ቃሎች፣ ተረትና ምሳሌዎች በቃል ደረጃ ያሉ ናቸው፡፡ እነዚህን ቀርጾ ማስቀመጥ ለዓይነ ሥውራን ብቻ ሳይሆን ለማንም የሚያስፈልግ ነገር መሆኑን ያብራራሉ፡፡በሌላ በኩል ቤተ መጻሕፍት ውስጥ የዕድሜ ባለጸጎች ሀሳብም መቀመጥ እንዳለበት ያሳስባሉ፡፡ ‹‹አዛውንት ተንቀሳቃሽ ቤተ መጻሕፍት ናቸው›› የሚለው ለምን በወሬ ብቻ ይሆናል? ሲሉም ይጠይቃሉ፡፡ ቤተ መጻሕፍት ናቸው ከተባለ የእነዚህ ሰዎች ሀሳብ ተቀርጾ መቀመጥ አለበት፤ ሰዎቹ ያልፋሉ፤ እውቀታቸው ግን አያልፍምና ተሰንዶ መቀመጥ አለበት፡፡የተማሩ የሚባሉት ራሳቸውም ይጽፉት ይሆናል፡፡ ገጠር ውስጥ ያሉ ብዙ ነገር የሚያውቁ ትልልቅ አባቶች አሉ፡፡ የእነዚህ አባቶች እውቀት ተቀርጾ መቀመጥ አለበት፡፡ ለዓይነ ሥውራን ብቻ ሳይሆን ለማንኛውም ሰው በድምጽ የተቀመጠ መረጃ አስፈላጊ ነው፡፡ አገርኛ ተረቶችና ስነ ቃሎች አለመሰናዳታቸውም ያሳዝናቸዋል፡፡እንደ አቶ ተስፋዬ እምነት አንድ መጽሐፍ በድምጽ ሲተረክ የበለጠ አንባቢን ይፈጥራል እንጂ መጽሐፍ እንዳይሸጥ አያደርግም፡፡ ፍቅር እስከ መቃብርን ምሳሌ ያነሳሉ፡፡ ፍቅር እስከመቃብር በብዛት የተሸጠው ከተተረከ በኋላ ነው፡፡\nየተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መሥራች አቶ እዝራ እጅጉ ‹‹የኤርትራ ጉዳይ›› የተሰኘውን የአምባሳደር ዘውዴ ረታን ግዙፍ መጽሐፍ እና የአገር ባለውለታ ሰዎችን ግለ ታሪክ በድምጽ እንዲተረክ አድርጎ በሲዲ አሳትሟል፡፡ እዝራ ይህን በማድረጉ እድለኛ እንደሆነ ይሰማዋል፡፡የድምጽ ቤተ መጻሕፍት እንዲጀመር አነቃቂ ይሆናል ብሎም ያስባል፡፡ ሥራውን አይቶታልና መሥራት እንደሚቻልም ይመሰክራል፡፡ ይህ ሲሆን ግን መገናኛ ብዙኃን ላይ አንድ ችግር መኖሩን ይጠቅሳል፡፡ የክምችት ክፍላቸው በአግባቡ ጥቅም ላይ አይውልም፤ ለሰው ለመስጠትም ፈቃደኞች አይደሉም፡፡ ከ50 ዓመት በላይ የቆዩ ክምችት ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን ብዙ ናቸው፡፡ የመሪዎች ድምጽ፣ የተለያዩ ታዋቂ ሰዎች ግለታሪክ አላቸው፤ ግን ይሄ ወደ ህዝብ እንዲደርስ አልተሰራበትም፡፡ በመሆኑም ህጋዊ በሆነ አሰራር ከመገናኛ ብዙኃን የክምችት ክፍል መገዛት እንዳለበት እዝራ ያሳስባል፡፡በውይይቱ ላይ በርካታ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት ቤተ መጻሕፍት ውስጥ የድምጽ ክምችት ክፍል የሚያስፈልገው ለዓይነ ሥውራን ብቻ አይደለም፡፡ ከማንበብ ይልቅ በመስማት ሀሳብን መያዝ የሚፈልግም ይኖራል፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎችና ሌሎች ሰራተኞችም ሥራ ሳይፈቱ እውቀትን ማግኘት ይችላሉ፡፡ በዋናነት ግን ለዓይነ ሥውራን ደግሞ የበለጠ ታስቦበት ሊሰራ እንደሚገባም ያሳስባሉ፡፡ወጣት ሲሳይ ሰማኸኝ የችግሩን አስከፊነት እንዲህ ይናገራል፡፡ ‹‹በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 አዲስ ዜማ የሚባል ፕሮግራም አለ፡፡ በዚህ ፕሮግራም ላይ መጽሐፍ ተቀንጭቦ ይተረካል፡፡ ያንን ትረካ ከሰማሁ በኋላ መጽሐፉን ማንበብ የበለጠ ያጓጓኛል፤ ሃሳቡ ተቀንጭቦ በመቅረቡ የባሰ ውስጤ ተረብሾ ይቀራል። በመሆኑ መተረክ ካለበት ተሟልቶ ነው መተረክ ያለበት››የብሄራዊ ቤተ መጻሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ይኩኑአምላክ መዝገቡ እንደሚሉት በቤተ መጻሕፍቱ ውስጥ ያለው የዓይነ ሥውራን ቤተ መጻሕፍት ለይስሙላ ብቻ ነው፡፡ የብሬል መጻሕፍት ቢኖሩም በቁጥር አነስተኛ ናቸው፡፡ አሁን የታሰበው ነገር መጻሕፍትን በድምጽ የማስቀመጥ ሥራን ማስፋፋት ነው፡፡የሚያነቡትም ከዚህ በፊት የመተረክ ልምድ ያላቸው የጥበብ ሰዎች ናቸው፡፡ በቀጣይ ይህን አጠናክሮ ለመሥራት ከደራሲዎች፣ ከተራኪዎችና ሆነ ከመገናኛ ብዙኃን ጋር ከባለቤትነት መብት ጋር ባለው የአሰራር ደንብ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 21/2011\nበዋለልኝ አየለ", "passage_id": "1c0e137a4c3a24b1bdfce28301f9c4e4" } ]
525622b024630e4b6f3639a1a8fa434f
af937c8d69cad649811e8ac5199a6610
ቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተጨማሪ ባለሀብቶችን ለመቀበል ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ተገለጸ
ዳግማዊት ግርማአዲስ አበባ፡- የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተጨማሪ ባለሀብቶችን ለመቀበል ዝግጅቱን መጨረሱን የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የአዲስ አበባ ማስተባበርያ ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የማስተባበርያ ፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ያየህ አዲስ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የነበሩበትን ችግሮች ቀርፎ ለባለሀብቱ ምቹ ሁኔታዎችን እየፈጠረ፤ በፓርኩ ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሀብቶችም የተሻሉ ማበረታቻዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ለኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚውሉ ግብአቶች በአካባቢው የሚገኙ መሆናቸው ለባለሀብቶች ትልቅ ዕድል መሆኑን የተናገሩት አቶ ያየህ፤ በስፍራው ያለው ሰላማዊ እንቅስቃሴም ለባለሀብቶች ምቹ እንቅስቃሴን የሚፈጥር መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ኢንዱስትሪ ፓርኩ የመሰረተ – ልማት ችግር እንደነበረበት ያወሱት ኃላፊው፤ በአሁኑ ጊዜ ግን የአስፓልት መንገድ መሠራቱን፣ የመብራት አገልግሎት መኖሩን፣ ለሥራ የሚሆን መሬትም ተዘጋጅቶ ማለቁን እንዲሁም ለትምህርት ቤቶች እና ለሌሎች አገልግሎት የሚውሉ ስፍራዎች ተሠርተው መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡ፓርኩ 600 ሄክታር ላይ ያረፈ ሲሆን፤ ከዚህም 200 ሄክታር ያህሉ መልማት መቻሉን፤ ከለማው መሬት ውስጥም 100 ሄክታሩ ለባለሀብት መሰጠቱን፤ እንዲሁም መሬት ከያዙት ባለሀብቶችም ሥራ የጀመሩ እንዳሉና በአግሮ ኢንዱስትሪ ስር የሚገኘው አንድ የዘይት ፋብሪካም በቅርቡ ሥራ እንደሚጀምር ነው አቶ ያየህ የገለጹት፡ የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚፈልጋቸው ባለሀብቶች በምግብና ምግብ ነክ ቁሳቁሶች ላይ መሥራት የሚፈልጉና ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚችሉ መሆኑን በመግለጽ፤ የክልሉ ኢንቨስትመንት ቢሮም የበለጠ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየሠራ እንደሆነ እና በክልሉ ውስጥ የመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ባለሀብቶች ከወዲሁ ዝግጅት እዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡አግሮ ኢንዱስትሪዉ ከፍተኛ የሆነ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ማዕከል ለመሆን እንዲሁም በክልሉ የሚገኘውን የእርሻ ምርት ውጤት በተሻለ ጥራት እሴት ጨምሮ ለመላክ የሚያስችል ሲሆን፤ ኢንዱስትሪዉ ሙሉ ሥራውን ሲጀምር ከ10ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርም አቶ ያየህ አዲስ ተናግረዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ፣ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37598
[ { "passage": "በአገሪቱ በአራት ክልሎች የሚቋቋሙት የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮች  ከ400ሺ በላይ  ለሚሆኑ ዜጎች   የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ ።በሚኒስቴሩ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አሰፋ ተስፋዬ ለዋሚኮ እንደገለጹት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦላቸው የግንባታ ሥራቸውን ለማስጀመር እንቅስቃሴ  እየተካሄደባቸው ያሉት አራት ሞዴል የተቀናጁ  የአግሮ ኢንዱስትሪ  ፓርኮች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አላቸው ።ሞዴል አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ በአማራ ክልል በቡሬ አካባቢ ፣ በትግራይ በሁመራ ፣ በኦሮሚያ አዳሜ ቱሉና በደቡብ ክልል በይርጋለም አካባቢ  የሚገነቡ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አሰፋ ለግንባታ ሥራው  የሚውለውን  1ሺ ሄክታር መሬት  እያንዳንዱ ክልል አቅርቧል ብለዋል ።በአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮቹን ውስጥ የሚገቡት 80በመቶ የሚሆኑት የአገር ውስጥ  ባለሃብቶች እንደሚሆኑ የጠቀሱት አቶ  አሰፋ 20 በመቶ  የውጭ አገር ባለሃብቶች  በፓርኮቹ ገብተው እንዲሠሩ ይፈቀዳል ብለዋል ።መንግሥት አራቱን የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለማስገንባት ከዘላቂ ልማት ግብ ፈንድ   የ250 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገንዘብ አግኝቷል ያሉት አቶ አሰፋ ሁሉም ክልሎች ለፓርኮቹ ግንባታ  የሚውል ገንዘብም እንደሚመድቡ አክለው ገልጸዋል ።የሚገነቡት አግሮ ኢንዱስትሪዎች በውስጣቸው የምግብ ማቀነባባቂያ ኢንዱስሪዎች  ፣ በገጠር  ግብዓት ማቅረቢያና ግብዓት መሰብሰቢያ ማዕከላት ያካተቱ እንደሚሆኑ አቶ አሰፋ አመልክተዋል ።አግሮ ኢንዱስሪዎቹ በአካበቢያቸው የሚገኙት የግብርና ውጤቶችን በጥሬ እቃነት በመጠቀም  የሚያመርቱ ሲሆን  በፓርኮቹ አካባቢ እስከ 100  ኪሎሜትር የሚደርሱ አርሶ አደሮች  ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገምቷል ።መንግሥት የአምራች ዘርፉን ለማሳደግ በተለያዩ የኢንዱስትሪ ዘርፎች የመሠረተ ልማት  የተሟላላቸውን  የኢንዱስትሪ ፓርኮችን  በማስገንባት ላይ እንደሚገኝ  ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ዘግቧል ።          ", "passage_id": "5466e102ff02eab298ba6f086e7b00fe" }, { "passage": "አራት ክልሎች በመገንባት ላይ የሚገኙ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በታኅሣሥ መጨረሻ ለባለሀብቶች እንደሚተላለፉ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።«ክልሎች ባልተጠና መልኩ ሕገወጥ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ መጀመራቸውም አስግቶኛል››ብሏል።በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ አያልነህ አባዋ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ ግብርናውን ከኢንዱስትሪ ጋር በማስተሳሰር ከጥምረቱ ፍሬ ተጠቃሚ ለመሆን በ2009 ዓ.ም የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ተጀምሯል።ለዚህም 17 ቀጣናዎች የተለዩ ሲሆን፤ በፓይለት ፕሮጀክት ደረጃ የጥሬ ዕቃዎች ምርት መገኛ መሆናቸውን መሠረት በማድረግ የመጀመሪያዎቹ ፓርኮች ግንባታ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይና በደቡብ ክልል ተግባራዊ ተደርጓል።ባለፉት ዓመታትም ፓርኮቹን ገንብቶ ሥራ ለማስጀመር የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን የገለፁት አቶ አያልነህ፤ በአሁኑ ወቅት ፓርኮቹን ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችሉ መሠረታዊ ግንባታዎች መጠናቀቃቸውንና በመጪው ታኅሣሥ መጨረሻ ለባለሀብቶች እንደሚተላለፉም ጠቁመዋል።አቶ አያልነህ በፓርኮቹ ውስጥ የሚሰማሩ ብቃት ያላቸው ባለሀብቶችን በመመልመል ረገድ ጥናትና የሌሎች አገራት ተሞክሮ የመቃኘት ተግባር በጥንቃቄና በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አመላክተዋል።በአሁኑ ወቅትም ወደ ፓርኮቹ ለመግባት በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ባለሀብቶች ተመዝግበው እየተጠባበቁ እንደሚገኙ የጠቆሙት አቶ አያልነህ፤ ቀደም ብለው ወደ ሥራ በመግባት ማምረትና ግንባታ የጀመሩ ስለመኖራቸውም አስታውቀዋል።የፓርኮቹ ግንባታ የተጀመረው በተመሳሳይ ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው፤ በበጀት እጥረት የትግራይ ክልል ወደ ኋላ መቅረቱንና አንዳንድ ግንባታዎች አለመጀመራቸውንም አብራርተዋል።‹‹የኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ዋነኛ ፈተና የኤሌክትሪክ ኃይል እጦት ነው›› ያሉት አቶ አያልነህ፣ በአሁኑ ወቅት በፓርኮቹ ሥራ የጀመሩ ባለሀብቶችም ቢሆኑ  በእራሳቸው አቅም ለችግሩ መፍትሄ ለመስጠት ወስነው የገቡበት መሆናቸውን ጠቁመዋል።ከችግሩ አሳሳቢነት አንፃር ድርድር ተካሂዶ አቅርቦቱን ለማፋጠን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ጉዳዩ ግን ልዩ ትኩረት እንደሚሻው አስገንዝበዋል።‹‹ከኃይል አቅርቦቱ በተጓዳኝ በአሁኑ ወቅት ከፌዴራል መንግሥት እውቅና ውጪ አንዳንድ ክልሎች የፓርኮች ግንባታ እያከናወኑ መሆናቸው በጣም ያሳስበናል›› ያሉት አቶ አያልነህ፣ አንዳንዶቹ ክልሎችም ተጨማሪ ፓርክ ለመገንባት ቦታ ከመምረጥ ባለፈ በልማቱ ለሚነሱ አርሶ አደሮች ካሳ ከፍለው መጨረሳቸውን አስታውቀዋል። ", "passage_id": "65fc4f5a52379f9cbcc48688a01f3171" }, { "passage": "ከ4 ሺህ በላይ የሚሆኑ የሀገር መከላከያና የፖሊስ ሰራዊት አባላት የአንድነት ፓርክን ጎበኝተዋል፡፡በደማቅ ሁኔታ ተመርቆ የተከፈተው የአንድነት ፓርክ በ2 ሺህ የሃገር መከላከያ እና በ2 ሺህ የፖሊስ ሰራዊት አባላትን በማስጎብኘት ስራውን በይፋ ጀምሯል፡፡መደበኛ የክፍያ ጉብኝት ከሚጀምርበት ከመጪው ሰኞ በፊት ፓርኩን እንዲጎበኙ ከተመረጡት የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ የሃገር መከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊት አባላት በፓርኩ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የቱሪስት መስህቦችን ተዟዙረው ሲጎበኙ ውለዋል፡፡በመጪዎቹ ሁለት ቀናትም አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን፣ የጎዳና ተዳዳሪዎች እና ታዳጊ ህፃናት ፓርኩን ቅድሚያ ወስደው ከሚጎበኙት የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ ይገኙበታል ተብሏል፡፡የአንድነት ፓርክን ለመጎብኘት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ይዞ መገኘት ሲኖርበት በተጨማሪም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቅድመሁኔታዎች ካላሟሉ ፓርኩን መጎብኘት አይችሉም።የሚከለከልጎብኚዎች ይዘው መምጣት የሌለባቸው ነገሮች።\n– ስለት\n– ተቀጣጣይ ቁሶች\n– የጦር መሳሪያዎች\n– ምግብ መጠጦች እና ጣፋጭ ነገሮች\n– ማስቲካ\n– የመዋቢያ ቁሶች\n– የግል ካሜራዎች\n– ስልኮች ታብሌቶች እና ማንቸውንም የምስልና ድምጽ መቅረጫ መሳሪያዎችን\n– ሲጋራ እና አደንዛዥ ዕጾችስነምግባርበፓርኩ ውስጥ ማድረግ የተከለከሉ ተግባራትና ባህሪያት።\n– መጮህና መረበሽ\n– ከአስጎብኚ ውጪና ከተመደቡበት የጉብኝት ቡድን ውጪ መንቀሳቀስ\n– በታሪካዊ ህንጻዎቹ ላይ መደገፍ\n– ቅርሶችንና እንስሳትን መነካካት\n– እንስሳትን ከተፈቀደው ቦታ ውጪ መቅረብ\n– እንስሳትን መመገብ\n– እንስሳትን ማስቆጣት (ጠጠር መወርወር፣ በአካላዊ እንቅስቃሴ ማስፈራራት፣ አላስፈላጊ ድምጽ ማውጣት)\n– ከተቀመጡ የቆሻሻ ማስወገጃ እቃ ውጪ ቆሻሻ መጣል\n– ሲጋራና ሌሎች አደንዛዥ እጾችን መጠቀም\n– የቤት እንስሳትን ይዞ መምጣት\n– መንገድ ከተበጀለት ዉጪ መራመድ እና አጥሮችን ከልክ በላይ መጠጋትም ሆነ መደገፍ\n– ማንኛዉንም በ ፓርኩ የሚገኝ የኤሌትሮኒክስ ቁስ ያለፍቃድ መንካት(ምንጭ፡-አንድነት ፓርክ)", "passage_id": "09e950fe2a7c588872948afae3342169" }, { "passage": "የሱዳን ባለሃብቶች የቦሌ ለሚን እና የቂሊንጦን ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ጎብኝተዋል፡፡ባለሃብቶቹ በኢትዮ-ሱዳን የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ለመሳተፍ የመጡ ሲሆን በጉብኝታቸውም ወቅት በፓርኮቹ አመራሮች ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡በፓርኮቹ ባዩት ነገር መደሰታቸውን ባለሃብቶቹ ገልጸው በቀጣይም ፋብሪካዎች የመገንባት ሃሳብ እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ሽፈራው ጃርሶ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ላይ ያከናወነችው ተግባር ስኬታማነት  የውጭ ባለሃብቶችን ቀልብ እየሳበ እንዲመጣ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሃገሪቱ ኢንቨስት ለማድረግ ለሚመጡ ባለሃብቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አምባሳደሩ አስረድተዋል፡፡", "passage_id": "eed78780cc5e64f5971077d8ea3433a0" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሱዳን ባለሃብቶች የልዑካን ቡድን በዛሬው እለት በምዕራብ አርሲ ዞን ጉብኝት አድርጓል፡፡\nልዑኩ ዛሬ በዞኑ የሚገኙ የአብጃታ ሻላ ብሔራዊ ፓርክና የላንጋኖ ሐይቅ መጎብኘቱን ኦቢኤን ዘግቧል፡፡ቀደም ባለው ቀንም በቢሾፍቱ የሚገኙ ሪዞርቶችን መጎብኘቱ ይታወሳል፡፡የኦሮሞያ ክልል ቆይታውን ካጠናቀቀ በኋላም ከገበታ ለሀገር ኢንቨስትመንት ጋር የሚተሳሰር ልማት ሥራ ላይ ለመሳተፍ አርባምንጭ ከተማ ገብቷል።የልዑካን ቡድኑ አርባምንጭ ከተማ ሲገባ የጋሞ ዞን፣ የአርባምንጭ ከተማ እና የአርባምንጭ ዙሪያ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውለታል።30 የሚሆኑ የሱዳን ባለሀብቶችን ከኩሪፍቱ ሪዞርት ጋር በመተባበር ከገበታ ለሀገር ኢንቨስትመንት ጋር የሚተሳሰር ልማት ሥራ ላይ ለመሳተፍ ነው አርባምንጭ ከተማ የገቡት፡፡ባለሀብቶቹ በዞኑ የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ከጎበኙ በኋላ ለማልማት ፍለጎታቸውን ያሳያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጋሞ ዞን ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡", "passage_id": "05294f4392ceb73bc05b9d3231ca7a03" } ]
203d7a76d64706ed382a9c45db9c3add
bec2fd989735fdce95318aeb93807dbc
“ከጁንታው ጎን ተሰልፈው ሀገርን ለማተራመስ የሚሠሩ የውጭ ኃይሎችን በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መታገል ይገባል” – ኦባንግ ሜቶ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች
 ጽጌረዳ ጫንያለውአዲስ አበባ፡- ከህወሓት ጁንታ ጎን ተሰልፈው ሀገርን ለማተራመስ የሚጥሩ የምዕራባውያን ጁንታዎችን ሴራ ለማጋለጥ በኢትዮጵያዊነት ስሜት በመቆም መታገል እንደሚገባ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ ሜቶ ገለጹ። አቶ ኦባንግ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የእኔ ብሔር ብቻ ማለት ባለፉት 27 ዓመታት የወረስነውና ያሳደግነው አስተሳሰብ ነው። ይህ ደግሞ ለነጭ ጁንታዎች ተጠቃሚነት ሰፊ ዕድል የሰጠና ኢትዮጵያን የችግር ቋት ውስጥ የከተተ ነው። በመሆኑም ከብሔር አስተሳሰብ ወጥቶ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ቆሞ የነጭ ጁንታዎችን እጅ ማሳጠር ያስፈልጋል። በአሁኑ ወቅት አንዳንድ የውጭ ኃይሎች ከሚያስተላልፉት መልዕክት ጀምሮ ኢትዮጵያን ለማቆርቆዝ ያለመ ሥራ እየሠሩ ይገኛሉ ያሉት አቶ ኦባንግ፤ የነዚህን ኃይሎች ድርጊት ለማስቆም በቅንጅት መሥራት ካልተቻለ አደጋው የከፋ ይሆናል ብለዋል። የህወሓት ጁንታ በ27 ዓመታት የአገዛዝ ዘመኑ ከነጭ ጁንታዎች ጋር በመሆን አገሪቱን ለብዙ ችግር ዳርጓታል የሚሉት አቶ ኦባንግ፤ አሁንም ይህንን አሠራር ነጭ ጁንታዎች ይፈልጉታልና የተለያዩ ሪፖርቶችን ለህዝብ በማቅረብ ከህወሓት ጁንታ ጎን መሆናቸውን እያሳዩ መሁኑን ተናግረዋል። አቶ ኦባንግ እንደገለጹት፤ እነዚህ ነጭ ጁንታዎች በአገሪቱ የተፈጠረውን ግጭት መነሻ አድርገው የተሳሳተ ፕሮፓጋንዳ እየነዙ ይገኛሉ። በተለይም የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ መስለው የሌለና የሀሰት መረጃ ከመስጠት አንጻር ከባድ ችግር እየፈጠሩ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያ ህዝብ እውነታውን ስለሚያውቀው ይህንኑ እውነታ ለዓለም ማህበረሰብ ማሳወቅ አለበት። ለዚህ ደግሞ በተናጠል ሳይሆን በአንድ ሃሳብ በአንድነት መቆም ይገባል። በኢትዮጵያ ያለው ጉዳይ የኢትዮጵያ እንጂ የነጭ ጁንታዎች ጉዳይ እንዳልሆነ ግልጽ ነው ያሉት አቶ ኦባንግ፤ እነዚህ ነጭ ጁንታዎች ግን እኛ እናውቅላችኋለን በሚል እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ኦባንግ ገለጻ፤ አሁን አገር እያተራመሰ ያለው ጁንታ ቀደም ሲል ከእነዚህ ነጭ ጁንታዎች ጋር ወዳጅ ነበር። በዚህ የተነሳ ጁንታው ሀገር በሚመራበት ወቅት ይፈጽም የነበረውን አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ለማሳየት አይፈልጉም። አሁን ግን የህግ ማስከበር ሥራ ሲሠራ ጩኸታቸው ሁሉ ሰብዓዊ መብት ሆኗል። አሁን አሁን ደግሞ የግጭቱ ፈጣሪ መንግሥት እንደሆነ ለማሳየት ይሞክራሉ። ‹‹የሰብዓዊ መብት ጉዳይ የመንግሥታት ድጋፍ ጉዳይ ሳይሆን ሰው የመሆን ጉዳይ ነው›› የሚሉት አቶ ኦባንግ፤ ነጭ ጁንታዎች ግን ይህንን ትተው 27 ዓመት ሙሉ የነበረውን አሰቃቂ ሰብዓዊ ጥሰት ሳያነሱ ዛሬ እየሆነ ያለውን ይኮንናሉ ብለዋል። ይሄን የሚሉ ኃይሎች ደግሞ ማመዛዘን እንኳን የተሳናቸው ለመሆናቸው ብዙ ምክንያት መጥቀስ ይቻላል የሚሉት አቶ ኦባንግ፤ የግጭቱ ጀማሪ የህወሓት ጁንታ ስለመሆኑ ጁንታው እራሱ ምስክርነቱን ሰጥቶ እያለ እነርሱ ግን መንግሥት ዋሽቷል ብለው ሲያቀነቅኑ መታየታቸውን ገልጸዋል። ከዚህ አንጻር የእነርሱ ድጋፍ ለጁንታው እንጂ ለሰብዓዊነት አለመሆኑን ነው አቶ ኦባንግ የገለጹት። እንደ አቶ ኦባንግ ገለጻ፤ የአውሮፓ ህብረት በተለያየ መንገድ ጫና እያሳረፈ እንደሆነ እሙን ነው። ስለሆነም ይህንን መመከት የሚቻለው ጉዳዩ የአገር መሆኑን አምኖ በተቀናጀ መልኩ የአመለካከት ለውጥ ማምጣት ላይ በመሥራት ነው። ለዚህ ደግሞ መንግሥትን ጨምሮ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ጥልቅ ጥናት አድርገው ሁኔታውን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስረዳት አለባቸው። የማይወክለንንም ሃሳብ አይወክለንም ማለት ያስፈልጋል። የህወሓት ጁንታ ከሠራው ሥራ አንዱ የመደራጀትና ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ተግባራዊ እንዳይሆን ማድረግ ነው ያሉት አቶ ኦባንግ፤ አሁን ግን ይህ ኃይል በመደምሰሱ ትክክለኛ ፍትህና የሰብዓዊ መብት መከበርን ማረጋገጥ ይገባናል ብለዋል። ለዚህ ደግሞ ሁሉም በሚያውቀው ቋንቋ እውነታውን ማስረዳትና የኢትዮጵያን ገጽታ መገንባት ላይ መረባረብ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ያስፈልጋል፤ የነጭ ጁንታዎችን የረዘመ እጅ መቁረጥም ይገባል ብለዋል። በቅርቡ ወደ አሜሪካ አቅንተው የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ሲያስረዱ እንደቆዩና አሁንም በዚህ ሥራ ላይ እንደሆኑ የሚያነሱት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ፤ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች ከኮንግረንስ እስከ ቲንክ ታንክ ግሩፕ ድረስ ወርደው መሥራታቸውን ተናግረዋል። አሁንም ቢሆን ነጭ ጁንታዎች ጠንካራ የኢትዮጵያ መንግሥት እንዲኖር ስለማይፈልጉ እነርሱ እጃቸው እንዲያጥር በመሥራት ላይ እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። ሆኖም በግለሰቦች ደረጃ የሚደረገው እንቅስቃሴ በቂ ስላልሆነ ሁሉም በቻለው ሁሉ መሥራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ፣ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37602
[ { "passage": "\nጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ትናንት ምሽት በኦሮሚያ ክልል በምእራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በተፈጸመው ጥቃት የተሰማቸውን ሀዘን በገለጹበት መግለጫቸው ፣ በኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ ባለው ማንነትን መሠረት ባደረገው ጥቃት እጅግ ማዘኔን እገልጻለሁ ብለዋል።\nየኢትዮጵያ ጠላቶች፤ \"ወይ እኛ እንገዛለን፤ ወይ ሀገር አትኖርም\" ብለው ተነሥተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህም የጥፋት ዐቅማቸውን ሁሉ እየተጠቀሙ እንደሆነ አንስተዋል።\nለዚህ እየተጠቀሙበት ያለው ስልት ግራ ቀኝ የማያውቁ ሰዎችን እየሰበሰቡ በማሠልጠንና በማስታጠቅ በየአካባቢው ማንነትን መሠረት ያደረገ አረመኔያዊ ጥቃት ማድረስ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ተግባርም ሕዝቡ እንዲደናገጥ፣ እንዲፈራና በስሜት ያልተገባ ርምጃ እንዲወስድ ታልሞ የሚከናወን እንደሆነ ገልጸዋል፡፡\nጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እንዳሉት የጥፋት ኃይሎች ከውጭ ላኪዎቻቸውና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በሚገኙ ባልጠሩ አድር ባዮች ትብብር ነው በሕዝቡ ላይ አሳዛኝ ጥቃት እያደረሱየሚገኙት፡፡ “ሁኔታው እንደ መሪም እንደ ዜጋም ልብ ይሰብራል” ሲሉ የተሰማቸውን ሀዘንም ገልጸዋል።\nበመግለጫቸው “ይህ ግን ከመንገዳችን ወደኋላ፣ ከግባችን ወደ ሌላ አያደርገንም። ተስፋ ቆርጠን እንድናቆም፣ ተሸንፈን እንድናፈገፍግ አያደርገንም። ከምንጊዜውም በላይ ኃይላችንን አሰባስበን እንድንነሣ ያደርገናል እንጂ” ብለዋል።\n“መንግሥት ሁሉንም ዓይነት አማራጮች ተጠቅሞ የችግሩን ሰንኮፍ ይነቅለዋል” ያሉት ጠ/ሚ ዐቢይ የጸጥታ አካላት ጥቃቱ ወደተፈጸመበት አካባቢ ተሠማርተዋል ብለዋል። “ርምጃም እየወሰዱ ነው” ሲሉም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይም የሕዝባችንን ደኅንነት ለማስጠበቅ መንግሥት የመንግሥትነቱን ሥራ በቁርጥና በጽናት ይሠራል ብለዋል።\nሕዝቡ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት፣ ምሁራንና ሌሎችም፧ መንግሥት ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ የሚወስደውን ርምጃ በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።\n\n", "passage_id": "66906eee98b2558aa442bcb638dd4ea4" }, { "passage": "ከሰሞኑ በባህርዳር የተከሰተው ድርጊት የህዝቡን ታሪክ የማይመጥንና ያለፍነውን የመጠፋፋት ባህል ዳግም ወደኋላ የመለሰ አደገኛ ክስተት በመሆኑ ሁሉም በነቂስ ሊያወግዘውና ሊታገለው ይገባል – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንንምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች አስከሬን ሽኝት ባደረጉት ንግግር፤ ከሰሞኑ በባህርዳር የተሰተው ጥቃት በህይወትና ማህበራዊ ገጽታው ለተጎጂዎችና ለቤተሰቦች ለትግል አጋሮቻቸው እጅግ የከበደ ነው።ድርጊቱ የህዝቡን ታሪክ የማይመጥን በጭካኔ የታጀበ አረመኔያዊ ድርጊት ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በሃገሪቷ ከስልጣንና ጋር በተያያዘ የነበሩ የመጠፋፋት ባህሎች ዳግም ወደ ወደኋላ የመለሰ አደገኛ ክስተት በመሆኑ ሁሉም በነቂስ ሊያወግዘውና ሊታገለው ይገባል ብለዋል።ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የክልሉን ዘርፈ ብዙ ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመፍታት በጋራ ዓላማ ተጋምደው፣ በአመራር ቋንቋ ተላምደው፣ በጓዳዊ አስተሳሰብ ተራምደው፤ በሙሉ ተስፋ የተሰለፉትን የቁርጥ ቀን ልጆች በእንዲህ ዓይነት ጭካኔ ማጣት ለሁሉም የላቀው ፈተናና ጸጸት ነው ብለዋል።በመሆኑም መንግስትና መሪ ድርጅቱ ከህዝብ ጋር በመሆን ድርጊቱን ማውገዝ ብቻ ሳይሆን፤ የተሰውትን ጀግኖች ዓላማና በዘመን የማያልፍ አበርክቶቻቸውን ዳር እንዲደርስ ሁላቸንም በጽናት መጓዝ፣ መራመድና ማሳካት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል።በአገርና በክልል የተያዘውን የለውጥ አጀንዳ አጠናክሮ ለመቀጠል ዋነኛ ስራም የህግ የበላይነት በማስከበር ሰላምን በመገንባትና የኢኮኖሚ ማነቆዎቸን በመፍታት ልማቱን ማፋጠን ይገባል ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።ነገር ግን እኝህ ወሳኝ ስራዎችና ሌሎች አጀንዳዎችን ለመፈጸም ብዙ እድሎች እያሉ፤በተግባር ከእድሎቻችን እየራቅን የችግሮቻችነን እድድሜ እያራዘምን እንገኛለን ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ አዙሪት ለመውጣት ከስሜታዊነት፤ ከጀብደኛነት፤ ከግለኝነትና ራስን ብቻ ከማዳመጥ ወጥተን ወደ ከፍታ የሚወስዱንን ጥበቦች መከተል ማለትም ምክንያታዊነትን፤ በሌላው ጫማ ላይ ሆኖ ማሰብን ህግና ሰርዓትን ማክበርን አርቆ ተመልካችነትን መላበስ ይኖርብናል ብለዋል።የአማራ ክልል ህዝብም ከዚህ አኳያ ታሪኩን የሚመጥን ምህዋር ላይ በመሳፈር በውስጡ አቃፊነቱን በመላው ዓለም ላይ ተከባብሮ ሰፍቶና ሞልቶ የመኖር ባህሉን አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።ከዚህ ውጪ የሚራመዱ ሃሳቦችና አስተምሮዎች ህዝባችንን ከከፍታው የሚያወርዱት መሆኑን አውቆ በጥንቃቄ ሊያቸውና ሊመክታቸው ይገባልም ነው ያሉት።በባህርዳር ከተማና አካባቢዋ የባሰ ጉዳት እንዳይደርስና እንዳይከሰት በሂደትም በቁጥጥር ስር እንዲውል ላደረጉ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የጸጥታ አካላትና የመንግስት አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው፤ እንዲህ ዓይነቱ ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ህግና ስርዓት እንዲነግስ ጥሪ አስተላልፈዋል።በህይወት ያጣናቸው ወንድሞቻችን፤ ጀግኖቹ! ለቤተሰቦቻቸው ተገቢውን ጊዜ ሳይሰጡ፤ ስለመጪው ሀይወታቸው ሳያስቡ፤ በተለያዩ አጀንዳ ውስጥ ሆነው በድንገት ወድቀዋል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሟች ልጆቻቸውም ሆነ የቤተሰቦቻቸው ተስፋ ከቶውንም ቢሆን ሊጨልም አይገባውም ብለዋል።የክልሉ ህዝብ፣ መንግስትና የለወጥ አጋሮች ከጎናችሁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።ለሀገር አቀፍና ለክልል አቀፍ ተልዕኮዎች መሳካት ከልጅነታቸው እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ሲሰሩ የነበሩ የመከላከያ የጦር መኮንኖች ህልፈትና በስራ ላይ እያሉ ህይወታቸው ላለፈው የድርጅታቸው ከፍተኛ አመራሮች ህልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ", "passage_id": "9de8c1f65129b27f68ba031112713c22" }, { "passage": "ሀገራችን ኢትዮጵያ የህግ የበላይነት የሚሰፍንባት እንጂ የአረመኔዎች እና የወንበዴዎች ዋሻ አትሆንም!!!ከሀዲው የህወሃት ጁንታ ቡድን በሰሜን ዕዝ መከላከያ ሰራዊታችን እና በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈጸማቸውን የጭካኔ ተግባራት የሀገራችን ህዝቦች በሰላማዊ ሰልፎች እያወገዙት ይገኛሉ፡፡ መንግስት የጀመረው ህግ የማስከበር ዘመቻ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና አሸባሪው የጁንታው መሪዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ ህዝባችን ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ለአለምአቀፉ ማህበረሰብ ሴረኛው ቡድን የፈፀመውን የሀገር ክህደት ወንጀል በውል ለማሳወቅ በሰላማዊ ሰልፎች መልዕክቱን አስተላልፏል፤ እያስተላለፈም ይገኛል፡፡ዛሬ ህዝባችንን ከዳር ዳር ያስቆጣው የሰው በላው ቡድን የጭካኔ ተግባር ለዓመታት በህዝባችን ላይ ሲተገብረው የቆየዉ ጥንስስ ሴራ ነው፡፡ የባንዳው ቡድን በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ የፈፀመው አሳፋሪ የሀገር ክህደት ወንጀል፤ከበረሃ የጀመረና ለእውነተኛ ትግል የወጡ ወንድሞቻቸውን በተኙበት መረሸን እና ንጹሃን ታጋዮችን በሴራ ወንጅሎ ማጥፋት እንዲሁም የትግል ጓዶቻቸውን በመክዳት እያደገ የመጣ የባንዳነት የልምምድ ውጤት ነው፡፡ይህ የጥፋት ቡድን ከህዝባችን በዘረፈው ሀብት እንደ ኦነግ ሸኔ አይነት ጽንፈኛ ቡድኖችን አደራጅቶ የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች በማንነት ላይ ተመስርቶ ንጹሃን ዜጎችን በጭካኔ ጨፍጭፏል፡፡ በነዚህ ኢ-ሰብዓዊ የጥፋት እቅዶች ምንም አይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸው በርካታ ንፁሀን ዜጎች በጅምላ ተገድለዋል፣ ቤት ንብረታቸውን አጥተዋል፣ ህጻናት ያለአሳዳጊ፣ አዛውንቶች ያለጧሪ ቀርተዋል፡፡ በይበልጥ የህዝባችንን ቁጣ የቀሰቀሰና ኢትዮጵያን ያቆሰለ ጭፍጨፋ በዋና አጋሩ ኦነግ ሸኔ አማካኝነት በኦሮሚያ ምእራብ ወለጋ፣ በደቡብ ክልል ጉራ ፈርዳ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞኖች ንጹሃን ዜጎችን በጅምላ የፈጀ ከመሆኑም በላይ ጨቅላ ህጻናትን፣ ነፍሰ ጡር ሴቶችን ሳይቀር ፍጹም ሰብዓዊነት በጎደለው ጭካኔ ገድሏል፡፡የጥፋት ሀይሉ በተደጋጋሚ በንጹሃን ላይ ያካሄደው የእጅ አዙር ጭፍጨፋ ሀገር የማፍረስ እቅዱን ሊያሳካለት ባለመቻሉ ባሳለፍነው ሳምንት ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም የመጨረሻውን ቀይ መስመር አልፎ በሀገር ሉዓላዊነት ላይ ቀጥተኛ ጥቃት ፈጽሟል፡፡ ይህ በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ የተፈጸመው አሳፋሪው ተግባር መላውን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች እጅግ ያስቆጣ እና የፈፀመው የሽብር ተግባር የለየለት ደም አፍሳሽ ወንበዴ ቡድን እንደሆነ በገሃድ አሳይቷል፡፡", "passage_id": "f849bd6ee9d7235dd7bf86efb7f90f19" }, { "passage": "መንግሥት ከጀመረው ሕግ የማስከበር ዘመቻ ጎን ለጎን የሕወሓት ቡድን ይፈጽመዋል ያሉትን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ለዓለም አቀፉ ማኅበርሰብ ማሳወቅ ቀዳሚ ሥራው እንዲሆን የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ /አዴሃን/ ጠየቀ።ንቅናቄው ሰሞኑን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በተቆጣጠራቸው አንዳንድ ቦታዎች በመሄድ የሞራልና የስንቅ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል።\n\n", "passage_id": "99ebc261b6fea90a3ac191fbdb24a096" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለችግር ለተጋለጡ በውጭ አገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ድጋፍ በሚደረግበት ዙሪያ በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2012 ዓም ውይይት ተደርጓል።ውይይቱን በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ የተመራ ሲሆን፤ በውይይቱ የሰላም ሚኒስትር ደኤታ ፍሬአለም ሽባባው፣ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ፣ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ጆሃን ቦርግስታም፣ የተ.መ.ድ ኤጀንሲዎች በኢትዮጵያ አስተባባሪ ዶ/ር ካትሪን ሶዚ እና የአለም አቀፍ ስደተኞች ድርጅት የኢትዮጵያበተ.መ.ድ በወጣው መግለጫ እና በአፍሪካ ህብረት ኮሚኒኬ መሰረት የሰዎች እንቅስቅቃሴ በአሁኑ ስዓት ያለውን የኮሮና ወረርሽኝ ተጋላጭነትን እንደሚጨምር ሁሉም አካላት ግንዛቤ መያዝ እንደሚያስፈልግ በውይይቱ ተነስቷል።ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ስርጭት ከቀን ወደ ቀን በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ የመጣ በመሆኑ ዜጎች ባሉበት አገር አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገላቸው እንዲቆዩ ማድረግ የተሻለ አማራጭ እንደሚሆን ግንዛቤ ተይዟል።ለዚህም የሚመለከታቸው ዓለም አቀፍ እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ እና ኢትዮጵያም አለም አቀፉን ወረርሽኙን በመቆጣጠር ረገድ ተሳትፎዋ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።", "passage_id": "8ca12d1ee6b28b8fa742fdd15bfb8147" } ]
31f0acdeab873015cb7181123359c0ac
652b4dd6b1e8c6139964a6410e79018c
የዳይመንድ ሊግ ለውጥ ተቃውሞ እያስተናገደ ነው
የዓለም አትሌቲክስ በየጊዜው የሚያስተላልፋቸው አዳዲስ ውሳኔዎች የስፖርቱን ቤተሰብ በማስከፋት የቀጠለ ይመስላል።የዓለም አትሌቲክስ በራሱ በሚያጸድቃቸው ሃሳቦች በበርካቶች ዘንድ ተቃውሞም ይቀርብበታል፤ ይሁን እንጂ ተግባራዊ ከማድረግ ወደ ኋላ አላለም።ከእነዚህ መካከል አንዱ በዳይመንድ ሊግ ይካሄዱ የነበሩ ውድድሮች መቀነሳቸው ነው።ሃሳቡ በተነሳበት ወቅት ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካዊያን የስፖርት ማህበራት ተቃውሟቸውን ቢያሰሙም ተቀባይነት ሊያገኙ ሳይችሉ ወደ ውሳኔ ተቀይሯል።ከአዲሱ የፈረንጆች አመት ጀምሮም ከዳይመንድ ሊግ እንዲቀነሱ የተደረጉ ውድድሮችን ተከትሎ በርካቶች ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ።በተለይ የአሜሪካ አትሌቶች ለጥያቄ ያመቻቸው ዘንድ ማህበር በመመስረት ላይ የሚገኙ መሆኑን ሜይል ኦንላይን አስነብቧል።በርዝመት ዝላይ የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑ ክርስቲያን ቴይለር በጉዳዩ ላይ አትሌቶች መታገል እንዳለባቸው በማህበራዊ ገጾች በመጠቀም አትሌቶችን እያነሳሳ ይገኛል።አትሌቱ በመግለጫው ላይ ስፖርቱን እያጠፉት መሆኑን የጠቀሰ ሲሆን፤ ለአትሌቶች መብት መታገል እንደሚገባም ገልጧል።ስፖርቱ እንዲያድግም መሰል ድርጊቶች መቆም እንዳለባቸውም ነው ያመላከተው። የውድድሩ አዘጋጆች ውድድሮቹ በቴሌቪዥን ሲተላለፉ ሳቢ እና ማራኪ እንዲሆኑ በማሰብ የቀነሷቸው የውድድር አይነቶች ላይ የዓለም አትሌቲክስ አሸማጋይ የሆነ ሃሳብ ከማንሳት ይልቅ ድጋፉን መስጠቱ ያበሳጫቸው አትሌቶችም ደብዳቤ ለዓለም አቀፉ የበላይ አካል ጽፈዋል።‹‹ውድድሩ በዓለም ህዝብ ዘንድ ሳቢ እንዲሆን ለውጦች መዳረጋቸውንና ማስፈለጋቸውን ብናምንም የዓለም አትሌቲክስ ግን አትሌቶችን ከግንዛቤ ያስገባ አይመስልም።በውሳኔው ላይ አትሌቶች አስተያየት እንዲሰጡ አለመደረጉም  ትክክል አይደለም›› ሲሉም አክለዋል።ማህበሩን በርካታ አትሌቶች እየተቀላቀሉት ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል እንግሊዛዊያኑ የዓለም ቻምፒዮን ዲያና አሸር ስሚዝ እንዲሁም የቀድሞው ርዝመት ዝላይ አትሌት ጆናተን ኤድዋርድስ ይጠቀሳሉ።አንጋፋው አትሌት የዓለም አትሌቲክስ በርካታ ስህተቶችን በመስራት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።ሆኖም ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው አካል አስካሁንም የሰጠው ምላሽ ወይም አስተያየት የለም።አዲስ ዘመን ጥቅም4/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22483
[ { "passage": "በሳዑዲ በምግብ ቤቶች ሴቶችና ወንዶች አንድ በር እንዳይጠቀሙ በሚያግደው ሕግ ምክንያት ወንዶችና ሴቶች በማክዶናልድ ለየብቻቸው ሲገበያዩ\n\nከዚህ በፊት በምግብ ቤቶች ውስጥ ለሴቶችና ለቤተሰቦች አንድ በር፣ ለወንዶች ደግሞ ለብቻቸው ሌላ በር ማዘጋጀት የግድ ነበር።\n\nይህ ዕገዳ በበርካታ ምግብ ቤቶች፣ ካፌዎች፣ እንዲሁም ሌሎች የሕዝብ መሰብሰቢያ ሥፍራዎች ከአሁን በኋላ ተግባራዊ አይሆንም ተብሏል።\n\n• «ካሾግጂ ወዲያው ነበር የታነቀው» ቱርክ\n\n• የሳዑዲ ሴቶች መሪ ጨበጡ\n\nበሳዑዲ አረቢያ የተለያዩ ለውጦች እየተካሄዱ ቢሆንም የተቃውሞ ድምጻቸውን የሚያሰሙ ዜጎችንም ማፈኑን ቀጥሏል ብለው የሞሞግቱ የመብት ተሟጋቾች አሉ።\n\nበዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ የሳዑዲ ሴት ያለ ወንድ ፈቃድ ወይም አጃቢነት ከሀገር ውጪ መሄድ እንደምትችል ንጉሡ ባስተላለፉት ትዕዛዝ አስታውቀው ነበር።\n\nእ.ኤ.አ. በ2018 ደግሞ በሴት አሽከርካሪዎች ላይ ለአስርታት ተጥሎ የነበረው የማሽከርከር እገዳ መነሳቱ ይታወሳል። አሁንም ግን የመብት ተሟጋቾች በርካታ ሴት አግላይ የሆኑ ሕጎች እንዳሉ መሆናቸውን በማንሳት የተቃውሞ ድምጻቸውን ያሰማሉ።\n\nመንግሥት ይህንን ለውጥ እያካሄደ ባለበት ወቅት እንኳ በርካታ የሴት መብት ተሟጋቾች በእስር ላይ እንደሚገኙ አክለው ተናግረዋል።\n\nእሁድ እለት የሳዑዲ ከተሞች ሚኒስትር ምግብ ቤቶች በጾታ የተለየ መግቢያ በሮችን መጠቀም እንደማይገባቸው ተናግረዋል። ይህን ውሳኔ የንግድ ተቋማቱ ራሳቸው እንዲወስኑ ተትቷል ሲሉም አክለዋል።\n\n• ፈጣን ለውጥና ጭቆና በሳኡዲ አረቢያ \n\n• ሳዑዲ ሴቶች እንዳያሽከረክሩ ጥላ የነበረችውን እገዳ ልታነሳ ነው\n\nመሐመድ ቢን ሳልማን በ 2017 የልዑሉነቱን ዘውድ ከደፉ በኋላ እጅግ ወግ አጥባቂ የሆነውን የሳዑዲ አረቢያ ማህበረሰብ ክፍት ለማድረግ የተለያዩ እርምጃዎች እየወሰዱ ናቸው።\n\nእያደረጉ ያሉት ለውጥ ከበርካታ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ አድናቆትን ቢያገኝም አሁንም ግን ጭቆና እንዳለ የሚገልፁ አልጠፉም።\n\nእ.ኤ.አ. በ2018 ቱርክ በሚገኘው የሳዑዲ ኢምባሲ ውስጥ የተገደለው ጋዜጠኛ ጃማል ኻሾግጂ ጉዳይ የዓለም አቀፍ መንግሥታት በአንድነት ያወገዙት ተግባር ሆኖ ይጠቀሳል።\n\nጃማል ኻሾግጂ የሳዑዲ መንግሥትን የሚተቹ ጽሑፎችን በመጻፍ ይታወቅ ነበር።\n\n ", "passage_id": "8a3fbaf7e4ad872138153107787a391b" }, { "passage": "በኔብራስካ፣ ኦማሃ ነዋሪነቷን ያደረገችው ዳይመንድ ትምህርት ቤት ውስጥ የነበራትን ስራ ስታጣ ከጎኗ የነበረውም ጓደኛዋ ጄምስ ስከርሎክ ነበር።\n\nእሱም ሆነ ቤተሰቦቹ ወደ ቤታቸው ጋበዟት፤ የሚበሉትን በልተው፤ ቤት ያፈራውንም እንደቀማምሱም የቤተሰባችን አካል ነሽ አሏት። በህይወቷ ትልቅ ውለታ ውሎልኛል የምትለው ጄምስ ቤት አልባ ከመሆን አዳናት። \n\n\"መኖሪያ አጥቼ እሱም ሆነ ቤተሰቦቹ አለንልሽ ሲሉኝ፤ ከጓደኛዬ በላይ መሆኑን ተረዳሁኝ\" በማለት ለሬዲዮ ዋን ኒውስ ቢት የተናገረችው ዳይመንድ \"ወንድሜ ነበር\" ብላለች።\n\nዳይመንድና የ22 አመቱ ጄምስ ጎረቤቶች ነበሩ። \n\nየተገናኙትም በጋራ መኖሪያ ቤቶቻቸው (አፓርትመንታቸው) ግቢ ውስጥ በሚገኘው የመዋኛ ገንዳ ከሁለት አመታት በፊት ነበር።\n\nጄምስ ስራ ቦታ ይሸኛታል፤ የትምህርት ቤት ስራዎቿንም ያግዛታል። እስካሁንም ቢሆን ደብተሮቿ ላይ የሳላቸው ስዕሎች አሉ።\n\nበሚወዱት ጓደኞቹ ጁጁ የሚል ቅፅል ስም የተሰጠው ሲሆን በታናናሽ ወንድሞቹና እህቶቹ የሚወደድ፤ ከሁሉ ጋር የሚቀልድ እንደነበርም ዳይመንድ ትናገራለች። \n\nበግንባታ ሰራተኝነት ተቀጥሮ ይሰራ የነበረ ሲሆን የሰባት ወር ልጁንም ለመንከባከብና አትኩሮትም ለመስጠት በሚል ስራውን አቆመ። በአባትነቱም ይኮራ ነበር ትላለች ዳይመንድ \n\nየህፃን ልጁን የወደፊት ሁኔታ ምን ሊሆን ይችላል? የሚለውም ሁኔታ ስለሚያስጨንቀውም ነበር ጄምስ ለማህበራዊ ፍትህ መታገልን የመረጠው። \n\nበተለይም በነጭ ፖሊስ ተደፍቆ የተገደለውን ጆርጅ ፍሎይድን ሞት ተከትሎ የተነሱ የ'ብላክ ላይቭስ ማተር' ተቃውሞዎች ላይም በከፍተኛ ሁኔታ ድምፃቸውን ካሰሙት መካከል አንዱ ነው።\n\nነገር ግን ግንቦት 22፣ 2012 ዓ.ም ጄምስ እንደወጣ አልተመለሰም። \n\nየአንድ መጠጥ ቤት ባለቤት የሆነው ነጩ ጃኮብ ጋርድነር በሽጉጥ ተኩሶ እንደገደለውም የሚያሳይ ቪዲዮ ወጣ።\n\nጃኮብ ጋርድነር መጠጥ ቤቱ በር ላይ እየጠበቀ የነበረ ሲሆን፣ ጄምስ ከኋላው መጥቶ ሲይዘውም ሁለት ጊዜ በአየር ላይ ተኩሶ በማስከተል ጄምስን እንደመታው ታውቋል። ጄምስም በደረሰበት ጉዳት ህይወቱ አልፏል። \n\nየግዛቱ አቃቤ ህግ የመጠጥ ባለቤቱ ራሱን ለመከላከል በሚል ነው የተኮሰው ስለዚህ ክስ አልመሰርትበትም ብሏል። ነገር ግን የአይን እማኞች ጃኮብ ጋርድነርና አባቱ ተቃዋሚዎችን የዘረኛ ስድብ ሲሳደቡ እንደነበርና ሲያስፈራሩም በማየቱ ጄምስ ለመከላከል ነው ከኋላ የገባው ብለዋል።\n\nየህዝቡንም ቁጣ ተከትሎ አቃቤ ህጉ ከማህበረሰቡ የተውጣጣ ኮሚቴ ያዋቀረ ሲሆን ግለሰቡ ይከሰስ አይከሰስ በሚለውም ጉዳይ ላይ የሚወስኑ ይሆናል። የመጠጥ ቤቱ ባለቤት ጥፋተኛ ሆኖ ካገኙትም በግድያ ወንጀል እንዲሁም ፈቃዱ ያለፈበት የጦር መሳሪያ በመያዝ ክስ ይመሰረትበታል። \n\n\"ለውጥ መምጣት አለበት\"\n\nየኔብራስካዋ ኦማሃ የባለፈው ዓመት የህዝብ ቁጥር እንደሚያሳየው 77 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ ነጭ ነው።\n\nየጄምስ መሞትንም ተከትሎ የኔብራስካ አስተዳዳሪ ፒት ሪኬትስ ጥቁሩን ማህበረሰብ ባናገሩበትም ወቅትም ስሜት አልባ ንግግር ነው በሚል ብዙዎች አቋርጠው ወጥተዋል።\n\nጓደኛዋ ሲሞት ዳይመንድ በቦታው አልነበረችም፤ ከዚያ በፊትም በነበሩት የተቃውሞ ሰልፎችም እንዲሁ አልተሳተፈችም።\n\nየፖሊስ ጭካኔን ብትረዳም ፖለቲካዊ ተሳትፎዋ ግን የቀዘቀዘ ነበር።\n\nይህ ሁሉ ግን ጄምስ ሲሞት ተቀየረ። \" ጄምስን እንደ ወንድሜ ነው የምወደው። እሱን ማጣት ማለት ተሰምቶኝ የማያውቅ ኃዘንና ህመም እንዲሰማኝ ሆኗል\" በማለትም ተናግራለች።\n\nየቅርብ ጓደኛዋንም ሞት ተከትሎ የኮሮናቫይረስ መመሪያዎች ሳያስጨንቋት ከጓደኞቿ ጋር ተቃውሞውን ተቀላቀለች። \"መንግሥት በራሱ ህዝብ ላይ ተነስቷል\" የምትለው ዳይመንድ \"ህዝቡ ግን ከተባበረ... ", "passage_id": "a3fdd71c367bf875101ed2e27a20af68" }, { "passage": "ያለፈው የፈረንጆች መስከረም ወር የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ አነጋጋሪና ታሪካዊ ክስተቶችን ያስተናገደ ነበር። በተለይም በማራቶን ውድድር ኬንያዊው አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ በቬና ማራቶን ከሦስት ሳምንት በፊት ለማመን የሚከብደውን አርባ ሁለት ኪሎ ሜትር ከ2፡00 በታች ሮጦ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያሳየበት ውድድር አሁንም ድረስ መነጋገሪያነቱ ቀጥሏል፡፡ በሃያ አራት ሰዓት ልዩነት ውስጥ ሌላኛዋ ኬንያዊት ብሪጊድ ኮስጌ ቺካጎ ማራቶን ላይ ለአስራ ሰባት ዓመታት ሳይሰበር የቆየውን የዓለም ክብረወሰን ማሻሻሏ ታሪካዊና አነጋጋሪ ከመሆን አልፎ የውዝግቦች መነሻ ሆኗል፡፡ የውዝግቡ መነሻ ሁለቱ አትሌቶች የሰሩት ታሪክ ሳይሆን ታሪክ የሰሩበት የመሮጫ ጫማ ነው፡፡ ግዙፉ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ ማራቶንን ከ2፡00 በታች መሮጥ ይቻል ዘንድ ባለፉት ዓመታት ትልቅ ፕሮጀክት ቀርፆ ከኬንያዊው አትሌት ኪፕቾጌ ጋር በጋራ ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ይህም እንዲሳካ ፍጥነትን የሚጨምር ልዩ የመሮጫ ጫማ ከማዘጋጀት ጀምሮ ያልቆፈረው ጉድጓድ አልነበረም፡፡ ይህ ፕሮጀክቱ ተሳክቶም ኪፕቾጌ በአርባ አንድ አሯሯጮችና በዘመናዊው ጫማ ታግዞ አርባ ሁለት ኪሎ ሜትሩን 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማጠናቀቅ ችሏል፡፡ ሌላኛዋ ኬንያዊት ኮስጌም በቺካጎ ማራቶን በቅርብ ዓመታት ይሰበራል ተብሎ ያልተጠበቀውን የፓውላ ራድክሊፍ 2፡15፡25 የሆነ የዓለም ክብረወሰን በዘመናዊው የናይኪ ጫማ ሮጣ በሰማንያ አንድ ሰከንድ አንክታዋለች፡፡ ኪፕቾጌ ይህን ታሪክ ለመስራት ከሦስት ዓመት በፊት ሲነሳም ከተለያዩ የስፖርት ቤተሰቦች ተቃውሞ ማስተናገዱ አልቀረም። ማራቶንን የሰው ልጅ በተፈጥሯዊ መንገድ ከ2፡00 በታች ማጠናቀቅ እየቻለ በቴክኖሎጂ መታገዙ በበርካቶች ዘንድ አልተዋጠም ነበር፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ጀግኖች አትሌቶች ኃይሌ ገብረስላሴና ቀነኒሳ በቀለን ጨምሮ ማራቶንን በቴክኖሎጂ ታግዞ ከ2፡00 በታች መሮጥ እንደማይዋጥላቸው ይልቁንም በተፈጥሯዊ መንገድ ጠንካራ ዝግጅት ተደርጎ ሃሳቡን ማሳካት እንደሚቻል ገና ከውጥኑ ሲናገሩ ነበር፡፡ ኪፕቾጌ ያሳካው ፕሮጀክት በስፖርቱ ትልቅ መነቃቃትን ከመፍጠር ባሻገር የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ግንዛቤ ፈጥሯል፡፡ ይሁን እንጂ ይህን ስኬት በርካቶች ከስፖርታዊ ኩነቱ ነጥለው በመመልከት አትሌቱ ተጫምቶት የሮጠበትን የናይኪ ጫማ የማስተዋወቅ የንግድ ስራ አድርገው ተመልክተውታል፡፡ በንግዱ ዓለም ፍልስፍና ብዙ የሚዋጥ ባይሆንም ናይኪ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ በመላው ዓለም ትልቅ ስም እያለው በዚህ መንገድ ስፖርቱን ተጠቅሞ ምርቱን ለማስተዋወቅ መሞከሩ ሌሎች ተፎካካሪዎቹን ለመዋጥ ያደረገው ስግብግብነት እንደሆነ ያስቀመጡ ወገኖችም ጥቂት አይደሉም፡፡ የሰው ልጅ በተፈጥሯዊ መንገድ ሮጦ ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች ማጠናቀቅ እየቻለ ኪፕቾጌ በምቹ የውድድር ቦታ ላይ በረቀቀ ቴክኖሎጂ ታግዞ ማሳካቱ ከስፖርት መርህ ጋር ተቃራኒ እንደሆነ የሚያነሱም አሉ፡፡ በአርቴፊሽያል ነገሮች በአትሌቲክሱ መግባት ከጀመሩ ወደ ፊት ስፖርቱ አሁን ያለውን የፉክክር ለዛ ይዞ አይቀጥልም የሚል ስጋት ያላቸው የስፖርት ቤተሰቦች ከዚህም ከዚያም አትሌቲክሱ ላይ ጠንከራ ጥያቄና ትችት ሲሰነዝሩ ሰንብተዋል፡፡ ዛሬም ድረስ በበርካታ የቀድሞ የዓለማችን አትሌቶች ተቃውሞ እየገጠመውም ይገኛል፡፡ ዘ ታይምስ እንደ ዘገበው በርካታ አትሌቶች ናይኪ ባሰናዳው ዘመናዊ የመሮጫ ጫማ ላይ የተቃውሞ ድምፅ እያሰሙ ይገኛሉ። የቀድሞው ጣሊያናዊ የማራቶን ቻምፒዮን ጂያኒ ዲማዶናን ጨምሮ ሃያ አትሌቶች ተሰባስበው ለዓለም አትሌቲክስ የናይኪን ዘመናዊ ጫማ ተቃውመው ደብዳቤ አስገብተዋል፡፡ የዓለም አትሌቲክስ ህግ ‹‹የመሮጫ ጫማዎች አትሌቶች እግራቸው ላይ ጉዳት እንዳይደርስባቸውና በምቾት እንዲሮጡ እንጂ ተገቢ ያልሆነ ጥቅምና ድጋፍ እንዲያገኙ አይደለም›› ይላል፡፡ ኪፕቾጌ ማራቶንን ከ2፡00 በታች ሲያጠናቅቅ የተጫማው ጫማ ግን ናይኪ በቴክኖሎጂ የተጠበበትና ገና ለገበያ ያልዋለ እንደመሆኑ ልዩ ትቅም ወይም ድጋፍ አላገኘበትም ማለት አይቻልም፡፡ ኮስጌ በእንግሊዛዊቷ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ለአስራ ስድስት ዓመታት ተይዞ የቆየውን 2፡15፡25 ክብረወሰን በሰማንያ አንድ ሰከንድ ስታሻሽልም ይሄንኑ ጫማ አጥልቃ ነው የሮጠችው፡፡ ይህም መሮጫ ጫማ ፓውላ ራድክሊፍ ክብረወሰን ስትሰብር ከተጫመችው ከ60 እስከ 90 ሰከንድ አትሌቷን የማፍጠን ጥቅም ስላለው ያሻሻለችውን 81 ሰከንድ ላይ ጉልህ ተፅዕኖ እንደነበረው የተለያዩ ትንታኔዎች ወጥተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ዓለም አትሌቲክስ ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂዎች በተለይም ከመሮጫ ጫማው ጋር ተያይዞ ለአትሌቶች እገዛ ማድረግ አለባቸው የለባቸውም የሚለው ሃሳብ አከራካሪ መሆኑን ገልፃል፡፡ ስለዚህም ጫማው በአትሌቶች ፍጥነት ላይ የሚኖረውን ተፅዕኖ ለመመርመር አንድ የጥናት ቡድን ለማቋቋም ተገዷል፡፡ አትሌቶች በተለያዩ ጊዜዎች በሚመረቱ ጫማዎች ሮጠው የተለያዩ ክብረወሰኖችን ሲሰብሩ ቆይተዋል፡፡ ይህ የናይኪ አዲስ ጫማ ከገበያ አኳያ ብዙ ስለተወራለት እንጂ ከዚህ ቀደም የሌለ ነገር እንዳልሆነ የሚሞግቱ የአትሌቲክስ ቤተሰቦች ቁጥርም ቀላል አይደለም፡፡ እንደ ዘ ታይምስ ትንታኔ ከሆነ ናይኪ አዲስ ያመረተው ጫማ ለአንድ አንድ አትሌቶች ይፋ የተደረገው ከ2016 በፊት ነው፡፡ 2014 ላይ ዴኒስ ኪሜቶ በበርሊን ማራቶን 2፡2፡57 የሆነ የዓለም ክብረወሰን ሲያስመዘግብ ይህን ጫማ ተጫምቷል፡፡ ከዚያ በኋም አምስት ጊዜ ይህን ጫማ ያጠለቁ አትሌቶች ክብረወሰን አሻሽለዋል። ይህን ልብ ያሉት የፕሮፌሽናል አትሌቶች የብቃት አሰልጣኝ ስቲቭ ማግኔስ ‹‹ጥናቶችን ካስተዋልን ጫማው በአትሌቶች ፍጥነት ላይ ትልቅ ተፅዕኖ አለው›› በማለት ለዋሺንግተን ፖስት አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አዲስ ዘመን ጥቅምት24/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "cd169a8119d5071dcc10f893ddb937c8" }, { "passage": "- የማስደነስ ፈቃድ የሌላቸው ባሮችና የምሽት ክበቦች ይቀጣሉ- ፖሊስ ዳንስ ለግርግርና ለብጥብጥ ይዳርጋል ብሏል- 10 ሺህ ዜጎች የሚሳተፉበት የጎዳና ላይ የዳንስ ተቃውሞ ይደረጋል የአገሪቱ ዜጎች ህዝብ በተሰበሰበባቸውና በመዝናኛ ስፍራዎች የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በተመለከተ ገደብ የሚጥል አዋጅ አውጥቶ ሲተገብር የቆየው የስዊድን ፓርላማ፣ የአዋጁ አንድ አካል የሆነውና ህገ-ወጥ ዳንስን የሚከለክለውን አነጋጋሪ ህግ ተግባራዊ መደረጉን እንዲቀጥል መወሰኑን ዴይሊ ሜል ዘገበ፡፡የአገሪቱ ፖሊስም ህገወጥ ዳንስ፤ለግርግርና ብጥብጥ የሚዳርግ በመሆኑ ህጉን እንደሚደግፈው ያስታወቀ ሲሆን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው፤ አሳፋሪ የቢሮክራሲ መገለጫ በመሆኑ ሊሻር ይገባል ሲሉ ነቅፈውታል፡፡ ፓርላማው ድምጽ የሰጠበትና እንዲቀጥል የወሰነበት ይህ ህግ፣ ሙዚቃ ስለሰሙ ብቻ እግራቸውን ለዳንስ የሚያነሱ ግለሰቦችን በህገወጥነት የሚፈርጅ ሲሆን፣ የማስደነስ ፍቃድ የሌላቸው የባርና የምሽት ክለብ ባለቤቶች ሲያስደንሱ ከተገኙ እንደሚቀጡ ይደነግጋል፡፡ ደንበኞቻቸው በሰሙት ሙዚቃ ሁሉ ሳያቋርጡ ሲደንሱ ወይም ፈቃድ ሳያገኙ ሲውረገረጉ ከተገኙም የባርና የምሽት ክለብ ባለቤቶች እንደሚቀጡ ህጉ ይገልጻል፡፡ ህጉን የተቃወሙት አንድሪያስ ቫርቬስ የተባሉ ስዊድናዊ የምሽት ክለብ ባለቤት፣ ከዚህ በፊት እንደተደረገው ሁሉ በመጪው ነሐሴ ወር ላይ ህጉን የሚቃወም የጎዳና ላይ የዳንስ ተቃውሞ ለማድረግ  ማቀዳቸውን ተናግረዋል፡፡ በጎዳና ላይ ዳንሱ ከ10 ሺ በላይ ሰዎች ይሳተፋሉ ብለው እንደሚገምቱም ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "3c4713ea81bb42f15821b83dc1190f7d" }, { "passage": "የዓለም ታላቁ ስፖርታዊ ውድድር ኦሊም ፒክ፤ በየወቅቱ አዳዲስ የውድድር ዓይነቶችን በማካተት ይታወቃል። ፓሪስ\nበታሪኳ ለሶስተኛ ጊዜ እአአ በ2024 በምታስተናግደው ኦሊምፒክ ላይም አዳዲስ ውድድሮች የሚጨመሩ መሆኑ ታውቋል። የመጀመሪያው በማራቶን\nስፖርት ላይ መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውንም ሰው ማካተት ሲሆን፤ «ብሬክ» በመባል የሚታወቀው ዳንስ፣ በ«ስኬት ቦርድ» መንሸራተት፣\nበውሃ ላይ መንሳፈፍ እንዲሁም ተራራ መውጣት የኦሊምፒኩ የውድድር ዓይነቶች ናቸው።ከአትሌቲክስ ስፖርቶች ረጅሙን ርቀት የሚሸፍን ውድድር እንደመሆኑ ከፍተኛ ጽናትና ጥንካሬን ይጠይቃል፤ ማራቶን።\n42ኪሎ ሜትር መሸፈኑ ከባድ ቢያደርገውም በተለያዩ የዓለም ከተሞች በየሳምንቱ የሚካሄድ የውድድር ዓይነት በመሆኑ ብዙዎች ይሳተፉበታል።\nበተለይ በዚህ ርቀት እንደ ኦሊምፒክ ባሉ የውድድር መድረኮች ተሳትፎ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ከፍተኛ ክብርን ያስገኛል። በዚህም\nምክንያት በኦሊምፒክ የርቀቱ ተካፋይ የሚሆኑት፤ ታዋቂና ልምድ ያላቸው አትሌቶች ናቸው። በፓሪስ ኦሊምፒክ ላይ ግን የትኛውም መሮጥ የሚፈልግ ሰው ተካፋይ መሆን እንደሚችል የዓለም ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nአስታውቋል። ይህንን ዜና ተከትሎም የኦሊምፒኩን አስተባባሪ ኮሚቴ በፕሬዚዳንነት የሚመሩት ቶኒ ኢስታንጉዌት «ውድድሩን ልዩ ለማድረግ\nአንድ እርምጃ ተራምደናል። በርካቶችን የሚያሳትፉ የተለያዩ ውድድሮችም እንዲካተቱ አድርገናል። ተሳ ታፊዎች በየትኛውም ደረጃ ላይ\nቢገኙም በኦሊምፒኩ የተለየ ልምድ እንዲኖራቸው ማድረግ እንፈልጋለን» ሲሉ ገልጸዋል።በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ እአአ ከ1970 እንደተጀመረ የሚነገረው «ብሬክ» የተባለው የዳንስ ዓይነት፤\nባሳለፍነው ዓመት በቦነስ አይረስ በተካሄደው የወጣቶች ኦሊምፒክ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ አንድ የውድድር ዓይነት ተካሂዶ ነበር።\nይህንን ተከትሎም በዋናው የኦሊምፒክ ውድድር ላይም ለማካተት መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ ይጠቁማሉ።  ሊቀመንበሩ አክለውም\nከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲሁም የስፖርት ማህበራት ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኙና ልምዱ በሌሎች ስፖርቶችም እንዲንጸባረቅ\nእንደሚሹም ገልጸ ዋል።አዲስ ዘመን የካቲት\n18/2011ብርሃን ፈይሳ __\n  ", "passage_id": "f353ba31d75c252e4f49b91071931a2d" } ]
b51beeebc9e5b35635408d9be1060650
0831fa608e665eddf7a18af32f2a4656
የብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤት ማቋቋሚያ ጉባኤ ተካሄደ
 የብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤትን በአዲስ መልክ ለማቋቋም የሚረዳ መስራች ጉባኤ ተካሄደ። ምክር ቤቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 446/2011 ድንጋጌ መሰረትም የሃገሪቷን ስፖርት በበላይነት የሚመራ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ አደረጃጀት ወደ ተግባር ለመግባት እንደሚያስችልም ተጠቁሟል። የኢትዮጵያን ስፖርት ለመምራት ለኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር እንዲሁም ስፖርት ኮሚሽን ከተሰጠው ኃላፊነትና ተግባር ባሻገር በሚኒስትሮች ምክር ቤት የብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤት በማቋቋም ስፖርቱ ስለሚዳብርበት፣ ስለሚስፋፋበትና ስለሚመራበት ሁኔታ የተደነገገ መሆኑ ታውቋል።የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጉባኤውን በማስጀመር የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት መንግስት የተጠበቀውን ያህል ባይሆንም ለዘርፉ ድጋፉን ሲያደርግ ቆይቷል፤ ለወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። ዘርፉ በተለያዩ ጫና ዝግመታዊ ለውጥ ውስጥ መግባቱን ተከትሎ ችግሮች ቢስተዋሉም በውስን ስፖርቶች ግን አሁንም ሃገርን በማስጠራት ላይ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የስፖርት ዘርፍን ተወዳዳሪነት ለማላቅ፣ የህዝብ ኃላፊነትን ለማጎልበት፣ ዘርፉ እውቀት ባላቸው እንዲመራ የማድረግና ሁሉም ነገር በተወዳዳሪነት፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት እንዲሁም በውጤታማነት ብቻ መመራት እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል። እንደ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፃ በስፖርቱ ዘርፍ ፋይዳቸው ሚዛን በሚደፋ ጉዳዮች ላይ በማተኮር በህጻናትና ታዳጊዎች በማተኮር ሃብትና ጉልበት በሚጠይቀው ሁሉ ዘርፉን ማዘመን የግድ ነው። ምክር ቤቱም ከዚህ አኳያ ኃላፊነቱን ለመወጣት ተጠናክሮ ወደ ተግባራዊነት ሊገባ ይገባል። የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢዋ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው እንደገለፁት ምክር ቤቱ ምስረታ ስፖርቱ ደረጃውን በጠበቀና ወቅቱ በሚጠይቀው መልኩ እንዲመራ ያደርጋል። መንግሥት እስከ ታችኛው አደረጃጀት በመውረድና ከዘርፉ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት የሚያግዝ በመሆኑ በስፖርቱ የሚስተዋለውን ማነቆ ለመፍታት ያስችላል። ከዚህም ባለፈ ስፖርቱ ከእስካሁኑ በጠነከረ ሁኔታ እንዲጓዝ፣ አስተማማኝና ሰላማዊ ሆኖ እንዲካሄድ እንዲሁም ለኢኮኖሚው ጠንካራ መሰረት እንዲጥል የምክር ቤቱ መመስረት የሚረዳ መሆኑንም አብራርተዋል።ስፖርቱ በ1990 በተቀረጸው ፖሊሲ መሰረት ከመጓዝ ይልቅ በርካታ ስር ነቀል መፍትሄ የሚፈልጉ ችግሮች ያሉበት በመሆኑ እንዲሁም እንደሚጠበቀው በጥሩ ቁመና ላይ አለመገኘቱ አዲስ ፍኖተ ካርታ መቀረጹንም በማቋቋሚያ ጉባኤው ላይ ተገልጿል። በፍኖተ ካርታው ላይ እንደተገለጠው ከሆነም የስፖርት ፖሊሲው በአፈጻጸም በኩል ችግሮች እንዳሉበት ተጠቁሟል። ስፖርት አደረጃጀቱ ብቃትና ጠንካራ አለመሆን፣ የማህበረሰብ ስፖርት ተሳትፎ አናሳ መሆን፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ ትጥቅና ቁሳቁስ እጥረት፣ የስፖርት ባለሙያዎች ልማት ጥራትና አቅርቦት ችግር፣ የላቁ ስፖርተኞች ልየታና ልማት ችግሮች፣ ከስፖርት ውድድሮች፣፣ ከትምህርትና ምርምር ጋር ተያይዞ የሚታይ ችግር እንዲሁም እስካሁን ያልተሰራበት የስፖርት ለማህበራዊ ልማትና ለሃገር ብልጽግና አለማዋል ዋናዋናዎቹ ችግሮች መሆናቸው በሰነዱ ላይ ተዘርዝሯል።በመፍትሄ ሃሳብ ደረጃም በስፖርት ፖሊሲው ላይ ክለሳ ማድረግ፣ የአደረጃጀት ማሻሻያ፣ ዓለም አቀፍ ህግጋትን ህዝብ ወደሚረዳው ቋንቋ በመተርጎም ተደራሽ ማድረግ፣ የገንዘብ አቅርቦትና የሃብት ክምችትን ማሳደግ፣ የላቁ ስፖርተኞች ልየታ ልማት፣ የሃገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ተሳታፊነትን ማሳደግ፣ ዘመናዊ የስፖርት ትምህርትና ስልጠና መስጠት እንዲሁም ስፖርትን ለማህበራዊ ልማትና ለሃገር ብልጽግና ለማዋል የሚያስችሉ ዘዴዎችን ተግባራዊ ማድረግ የሚሉት ተጠቅሰዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም ብሔራዊ የስፖርት ሙዚየም መገንባት አስፈላጊ መሆኑም ተመልክቷል።የቀረበውን ፍኖተ ካርታ ተከትሎ በምክር በተሳታፊዎች ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል። በምክር ቤቱ ማቋቋሚያ የስፖርት ባለሙያዎችን ባካተተ መልኩ አለመሆኑ ቅሬታ የፈጠረ ሲሆን፤ የተጠሪና የፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የሥራ ድርሻ ተለይቶ በፍኖተ ካርታው ላይ መቅረብ እንዳለበት ተጠቁሟል። ይህ ችግርም ከዓለምና ሃገር አቀፍ ስፖርት ማህበራቱ ጋር ለመስራት ችግር እንደሆነበት እና ለአሰራር ምቹ እንዲሆን ራሱን መቻል እንደሚገባ ተገልጿል። መንግሥት ለሌላው ዘርፍ የሚሰጠውን አይነት ትኩረት መስጠት እንደሚገባውና ስፖርቱ ራሱን እስኪችል ማገዝ እንደሚገባም በውይይቱ ተሳታፊዎች ተነስቷል። የባለሃብቶች ተሳትፎ አናሳ መሆንን ተከትሎ በዘርፉ ተሳታፊ እንዲሆኑ ማበረታቻ ቢደረግ፣ ለትልልቅ ስታዲየሞች መተዳደሪያ የሚሆን ደንብ አለመኖር፣ ስፖርታዊ ውድድሮች የችግር ምክንያት በመሆናቸው በፍኖተ ካርታው ላይ አቅጣጫ ሊቀመጥለት እንደሚገባም ተጠይቋል። በፖሊሲው ላይ የህዝባዊ አደረጃጀቱ በአማተሮች እንዲመራ የሚጠቁም ቢሆንም ለስፖርቱ ውጤታማነት አመራሩ ከፊል ፕሮፌሽናል መሆን እንደሚገባውም ተገልጿል። በአካል ጉዳተኞች ዙሪያም ፍኖተ ካርታው የተሻለ ትኩረት እንዲሰጥ፣ ስፖርተኞች ማበረታቻ አለመኖር ከብሄራዊ ቡድን እያራቃቸው በመሆኑ ቢታሰብበት፣ በየክልሉ ያሉ ስታዲየሞች ደረጃ ከመስፈርት በታች በመሆኑ ትኩረት ቢሰጠው እንዲሁም ስፖርቱን ከሰላምና ጠና መድረክነቱ ባለፈ በቱሪዝምና ገቢ ማግኛ መንገድ ማሳደግ ቢቻል የሚሉ ሃሳቦች ተንጸባርቀዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም የተነሱ አስተያየቶችን በማካተት ሪፎርሙ እንደሚሻሻልም ተጠቁሟል።በማቋቋሚያ ጉባኤው ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ በሚኒስቴሩ የስፖርት ዘርፍ ዲኤታ አቶ ሃብታሙ ሲሳይ፣ የስፖርት ኮሚሽነሩ ኤልያስ ሽኩር፣ ምክትል ኮሚሽነሩ ጌታቸው ባልቻ፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ስፖርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ ሃገር አቀፍ ስፖርት ማህበራት ፕሬዚዳንቶችና የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች፣ ለስፖርቱ እድገት ጉልህ ሚና ያላቸው የክብር እንግዶችና ባለድርሻዎች ተገኝተዋል። አዲስ ዘመን ጥቅም5/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22532
[ { "passage": "ምስረታውን በ1985ዓም ያደረገው ኢትዮ ዩናይትድ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለው መከፋፈል መሰረት በኢትዮጵያም በሶስት አሶሴሽኖች ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። በኢትዮጵያ በተለይ በወጣቱ ዘንድ እጅግ ከተስፋፉ ስፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው ይህ የማርሻል አርት ስፖርት በፌዴሬሽን ደረጃ ለመደራጀትም ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን 2003ዓ.ም በወጣው የስፖርት ማህበራት ማቋቋሚያ መመሪያ መሰረትም የድሬዳዋ ኢትዮ ዩናይትድ ኢንተር ናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ሊመሰረት ችሏል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ስር የነበሩት ሶስት\nአሶሴሽኖችም በመጣመር ፌዴሬሽን ያቋቋመ ሁለተኛው ከተማ አስተዳደር ሆኗል። በፌዴሬሽኑ ማቋቋሚያ ጉባኤ ላይም የስፖርት ኮሚሽኑ ተወካይ\nአቶ መኮንን ገብረህይወት የፌዴሬሽኑን ምስረታ አብስረዋል። ተወካዩ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የአሰራር ሂደቱንና ደንቡን\nበተከተለ መልኩ የፌዴሬሽን ምስረታ መካሄዱን አረጋግጠዋል። ፌዴሬሽኑ በስድስት ክፍለ ከተሞች ውስጥ ብቃታቸው የተረጋገጠ 16 ክለቦችን\nያቀፈ፣ በ ‹‹ኤ ላይሰንስ›› ሁለት፣ በ ‹‹ቢ ላይሰንስ›› ስድስት፣ በ ‹‹ሲ ላይሰንስ›› አስር ዳኞች እንዲሁም ከ2-7ኛ ዳን\nያላቸው 16 አሰልጣኞች ያሉት በመሆኑ የማቋቋሚያ ጉባኤ ማድረግ የሚያስችላቸው መሆኑን ጠቁመዋል። በዚሁም መሰረት ስራ አስፈጻሚዎችን\nበመምረጥ ወደ ስራ እንዲገቡ፤ በሂደትም ጽህፈት ቤትና የስፖርት ማዘውተሪያ ገንብተው ከመንግስት ድጎማ እስኪላቀቁ በኮሚሽኑ ቢሮ\nእንዲሁም በትምህርትና ስልጠና ማዕከላት እንዲገለገሉ ፈቃድ ተሰጥቷል። በመጀመሪያው ጉባኤ ላይም አዲስ ፌዴሬሽን እንደመሆኑ ሪፖርት ማቅረብ ባይቻልም ቀጣይ እቅዶች ግን ለጉባየተኛው\nቀርበዋል። በዚህም የክለቦችን ቁጥር አሁን ካለበት ቁጥር ወደ 33 ማሳደግ፣ ጠንካራ ፌዴሬሽን እንዲሆን መስራት፣ ገቢውን በማሳደግ\nከኮሚሽኑ ድጋፍ የሚላቀቅበትን መሰረት መጣል፣ የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላትን ማሳደግ፣ ስፖርተኞችን በሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ\nውድድሮች ማሳተፍ፣ የተለያዩ ቻምፒዮናዎችን በማዘጋጀት ከተማ አስተዳደሩን እንዲሁም ሀገርን ለመወከል የሚችሉ ስፖርተኞችን ማፍራት፣\nበትምህርትና ስልጠና የዳኞችንና አሰልጣኞችን ቁጥር ወደ 100 ማሳደግ እንዲሁም በክትትልና ድጋፍ ላይ ለመስራት መታቀዱ ተገልጿል።\nገለጻውን ያዳመጠው ጉባኤም በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። በመተዳደሪያ ደንቡ ላይም ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ በጉባኤው አባላት ይሁንታ ሊያገኝ\nችሏል።ከተሳታፊዎች በተሰጠው አስተያየትም ስፖርቱ እስከ ወረዳ በመውረድ በይበልጥ እንዲስፋፋ ፌዴሬሽኑ ከክፍለ ከተሞች\nጋር በቅንጅት መስራት እንዳለበት እና ከመንግስት ድጎማ ለመላቀቅ የሚያስችለውን መንገድ ማፈላለግ እንዲሁም የሀብት አሰባሰብ ላይ\nማተኮር እንደሚገባው ተጠቁሟል። በተካሄደው የስራ አስፈጻሚዎች ምርጫም አቶ በቀለ በዳዳ በ14 ድምጽ በማሸነፋቸው ከቀድሞው የአሶሴሽኑ ፕሬዚዳንት\nኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሲኒየር ሳቦም ተሾመ አበበ የስራ ደንብና መመሪያ ተረክበዋል። አቶ መንሱር ጀማል ምክትል ፕሬዚደንት\nሲሆኑ፤ ወይዘሮ ሰብለወንጌል ቁምላቸው አቃቤ ነዋይ እንዲሁም ሌሎች አራት ግለሰቦች የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በመሆን ተመርጠዋል።\nተመራጮችም በጋራ በመሆን ስፖርቱን ለማሳደግ የሚሰሩ መሆኑን ቃል ገብተዋል። ከማርሻል አርት ስፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው ኢንተርናሽናል\nቴኳንዶ እአአ 1966 በጄኔራል ቾይ ሆንግ ሃይ ነው የተመሰረተው። የሁለቱን ኮሪያዎች መነጣጠል ተከትሎም ኢንተርናሽናልና ወርልድ\nቴኳንዶ በሚል ሲከፈል፤ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ በሰሜን ኮሪያ በስፋት ይከወናል። በሲኒየር ማስተር አብዲ ከድር መስራችነትም በኢትዮጵያ\nአሶሴሽኑ እስካሁን ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። በዚህ ወቅት የዓለም አቀፉ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን መቀመጫ በኦስትሪያ ቬና ሲሆን፤\nኢትዮጵያም አባል አገር ናት።አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 21/2012 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "f09ec51d75140a7e9ad31d454512eed4" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣መስከረም 25 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 5ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 6ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ስርዓት ጉባኤ ተካሄደ።ጉባኤው የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በሚገኘው የስብስባ አዳራሽ ነው የተካሄደው።የሁለቱ ምክር ቤቶችን የጋራ ስብሰባም የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ያስጀመሩት ሲሆን የ2013 የፌደራል መንግስቱ ልዩ ትኩረቶችን የሚዳስሰው የመክፈቻ ንግግራቸውን አቅርበዋል፡፡በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ታዋቂ ሰዎች እና አምባሳደሮች እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚገኙ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡ፕሬዚዳንቷ በመክፈቻ ንግግራቸው፦  #FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "093875e5f546f660c4f55e7aa80a9504" }, { "passage": "ጤናማ ስፖርተኛ ማፍራት ዓላማው ያደረገው የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ስፖርት ማኅበር 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓል በተለያዩ ፕሮግራሞች እየተከበረ ይገኛል።የዛሬ 25 ዓመት ምስረታውን ያደረገው የአዲስ አበባ ጤና ስፖርት ማኀበር የ25ኛ ዓመት በዓሉን መሠረት ያደረገ የተለያዩ ዝግጅቶችን ከጥር 3 –9 ቀን ድረስ እያከበረ ይገኛል። ዛሬ ከ08:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በርካታ የማኀበሩ አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የበዓሉ አንዱ አካል የሆነው ሲንፖዚየም ተካሂዷል።የማኅበሩ ፕሬዝደንት አቶ ተፈራ ደንበል የመክፈቻ ንግግር በማደረግ በተጀመረው በዚህ መድረክ “የስፖርት ጠቀሜታ” ምን እንደሆነ በአቶ ዘሪሁን ቢያድግልኝ አማካኝነት ጥናታዊ ፁሑፍ ቀርቧል። በጥናታዊ ፁሑፋቸውም ስፖርት ኀብረተሰብና ለማቀራረብ ፣ ጤና ኀብረተስብ ለመፍጠር እና በፖለቲካ የተራራቁ ህዝቦችን ለማቀራረብ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው በመግለፅ ይህን ስፖርት ለማስፋፋት ፣ ለማጠናከርና ውጤታማ ለማድረግ የስፖርት ፅንሠ ሀሳብና ጠቀሜታን ግንዛቤ መፍጠር፣ የስፖርቱን አደረጃጀት እስከ ታች ድረስ ወርዶ መዘርጋት፣ የአሠራር ስርዓቱንም በህጋዊ መንገድ መዘርጋት እና የስፖርት ማዘውተርያ ሥፍራን ማዘጋጀት ይገባል ብለዋል።በማስከተል ዶ/ር አያሌው ጥላሁን “የስፖርት እንቅስቃሴ ለጤንነት” በሚል ጥናታዊ ፁሑፍ አቅርበዋል። ስፖርት ለሁሉም ማኀበረሰብ ለጤንነት አስፈላጊ መሆኑ ገና በሀገራችን እንዳልዳበረ ብዙ መስራት እንደሚያስፈልገው ገልፀው። በዚህም ምክንያት ትንሽ ትልቁ ለተለያዩ በሽታዎች በመጋለጥ ጤንነት የጠፋው በስፖርት የዳበረ አካል መፍጠር ባለመቻሉ ነው። ከአካላዊ እንቅስቃሴ አለማድረጉ እንዳለ ሆኖ ከዚህ ባሻገር ከአመጋገብ፣ ከምንጠቀምባቸው መጠጦች እና ከአኗኗራችን ጋር ተያይዞ የሚመጡ የጤና እንከኖች በሀገራችን ተበራክተዋል ያሉት ዶ/ር አያሌው ለዚህም መፍትሔው ከበሽታ የነፃ፣ ሰውነቱን የተረዳና የሚቆጣጠር፣ ከመድሐኒቶች የነፃ፣ ከዓለም ጋር የሚጓዝ፣ ሩቅና ጥልቅ አሳቢ እና ፍላጎቱን የለየ ዜጋ ለመሆን ያሰበ ሰው የስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ አስፈላጊ ነው በማለት ፈገግ እያደረጉ በጨዋታ የተዋዛ ጠቀሜታ ያለው ሰፊ ማብራሪያ አቅርበዋል።በመቀጠል የአዲስ አበባ ጤና ስፖርት ማኅበርን የ25 ዓመት ጉዞ የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም ቀርቧል። በመጨረሻም ነገ ቅዳሜ ከ ጥር 9 ቀን ቄራ በሚገኘው አልማዝዬ ሜዳ ከጠዋቱ 02:00 ጀምሮ በሚከናውን የእግርኳስ ውድሮች የመዝጊያ ፕሮግራም የበዓሉ ፍፃሜ ይሆናል።", "passage_id": "14975672ce9a91de87a20fbceab4d6d0" }, { "passage": "ሙሉ ቀን በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የኢፌዴሪ ስፓርት ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት አቶ ርስቱ ይርዳውን ጨምሮ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደረሽን የስራ አስፈፃሚ አባላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የውይይት መድረኩን የከፈቱት የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ርስቱ ይርዳው እግርኳሱ በአሁኑ ወቅት ከሳምንት ሳምንት በጉጉት ከመናፈቅ ይልቅ ለሰዎች የስጋት ምንጭ እየሆነ መምጣቱን አውስተው ይህንን በስፓርቱ ላይ አሉታዊ ገዕታ እየፈጠረ የሚገኘውን ይህን የስፓርታዊ ጨዋነት መጎደል ችግርን ለመቅረፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚወጡት ድርሻ የላቀ በመሆኑ ይህንን የውይይት መድረክ ለማዘጋጀት መታሰቡን ገልፀዋል፡፡በመቀጠል ለውይይት መነሻ እንዲሆን በአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስ መምህር የሆኑት አቶ ሳሙኤል ስለሺ እና በሌሎች 9 የስፖርቱ ባለድርሻ አካላት በጋራ የተዘጋጀ ጥናታዊ ፅሁፍ በአቶ ስለሺ ለእድምተኞች ቀርቧል፡፡ ዘርዘር ያሉ ጉዳዮች በተዳሰሱበትና “ስፓርታዊ ጨዋነት፣ የተመልካች ረብሻ ሁከትና ብጥብጥ በኢትዮጵያ ወቅታዊ እግርኳስ” በተሰኘ ርዕስ በቀረበው ጥናታዊ ፅሁፍ የቀረቡት ዐቢይ ጉዳዮችን በሶስት መሠረታዊ ክፍሎች ተከፋፍሎ የቀረበ ነበር፡፡በፅሁፎ የመጀመሪያ ክፍል የጥናት ቡድኑ በአሁኑ ወቅት እየታዩ ባሉት የስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል ችግሮች መንስዔ ናቸው ያላቸውን ሀሳቦች በሶስት ክፍሎች በመክፈል ለመዳሰስ ተሞክሯል ፤ በዚህም ውስጥ እግርኳሳዊ ሙስና፣ ብሔርተኛ ክለቦች መበራከት እና የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በዋነኝነት በጥናት አቅራቢው እንደ መንስዔነት ተጠቅሰዋል፡፡በመቀጠልም በጥናታዊ ፅሁፉ የተዳሰሰው ጉዳይ ለእነዚህ መንስዔዎች በአቀጣጣይነት የጥናቱ ቡድኑ አገኘኋቸው ያላቸውን ሶስት አቀጣጣይ ምክንያቶችን አመላክቷል። እነዚህም የሜዳ ውስጥና ውጪ ያሉ ምክንያቶች እንዲሁም የስፖርት ሚዲያ እና መገናኛ ብዙሀን በሚል ሶስት ጥቅል አቀጣጣይ ምክያቶች ቀርበዋል፡፡ ከሜዳ ውጪ ባሉ ምክንያቶች ውስጥ መጠጥና እና ተያያዥ አደንዛዥ ዕፆች በስታዲየም ዙርያ መሸጥን ጨምሮ የፀጥታ ኃይል የተመለከተና ሌሎች ጉዳዮች የተዳሰሱ ሲሆን በሜዳ ውስጥ ምክንያትነት ደግሞ የዳኞችና ኮሚሽነሮች እንዲሁም የተጫዋቾችና የአሰልጣኞች ቡድን አባላት ቀርበዋል። የተጋነኑ ዘገባዎች፣ ለአካባቢ ቡድኖች ጥብቅና መቆም እና መሰል ምክንያቶች ደግም በመገናኛ ብዙሀን አቀጣጣይ ምክንያቶች ተብለው ቀርበዋል፡፡በጥናታዊ ፅሁፍ የመጨረሻ ክፍል ደግሞ በአጭር በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ውስጥ ሊከወኑ የሚገባቸውን የማስፈፀሚያና የመተግበሪያ ኃሳቦችን ለመዘርዘር ተሞክሯል ፤ በዚህም ጥናት አቅራቢው አፅንኦት የተሰጣቸው ነጥቦች የህግ ማዕቀፍና የሰነዶች ዝግጅት እንዲሁም በጊዜ ሂደት ተከፍፈለው የሚከወኑ የአዳዲስ አደረጃጀቶችና አሰራሮች ዙርያ ዘርዘር ያሉ የመፍትሔ ኃሳቦች ተጠቁመዋል፡፡በመቀጠል ውይይቱ ከሻይ እረፍት ሲመለስ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የቴሌቪዥን ዘርፍ ሃላፊ የሆኑት አቶ አቤል አዳሙ የስፖርት አዘጋገብ በሚል ሰፋ ያለ ገለፃ ተደርጓል። አቶ አቤል ባቀረቡት ገለፃ ላይም ካላቸው የስራ ልምድና ንድፈ ሀሳባዊ ጉዳዮች ጋር በማያያዝ ለመዳሰስ ሞክረዋል፡፡በመቀጠልም በአቶ ርስቱ ይርዳው፣ ኮሎኔል ዐወል እና አቶ ጌታቸው ባልቻ አወያይነት በቀጣይ የባለድርሻ አካላት ሚና ምን መምስል አለበት በሚል በተዘጋጀው ፅሁፍ ዙርያ ውይይት ተካሂዷል፡፡ ብዙሀኑ ተሳታፊዎች በጋራ የተስማሙበት ጉዳይ በብሔራዊ እግርኳስ ፌደሬሽኑና በክለቦች መካከል ያለው ያለመተማመን ስሜት በስፋት በተሳታፊዎች የተነሳ ጉዳይ ሆኗል። በተጨማሪም ፌዴሬሽኑን በተመለከተ በህግ አተረጓገም ላይ ያለ መላላትና የእርምጃዎች ተመጣጣኝነት ዙሪያ በርካታ ኃሳቦች ተነስተዋል፡፡ በተጨማሪም በፌዴሬሽኑ ስር ተመዝግበው እውቅና ተሰጥቷቸው የሚንቀሳቀሱ ክለቦች ስያሜንና አርማን እንዲቀይሩ የሚያደርግ አስገዳጅ ህጎችን ስለማውጣትና የስፖርታዊ ጨዋነትን የሚያበረታቱ ሽልማቶችን ማዘጋጀት የሚሉ ኃሳቦችም ተነስተዋል፡፡በተነሱት ሀሳቦች ዙሪያ ምላሻቸው የሰጡት የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ኮሎኔል ዐወል አብዱራሂም ” በቅርቡ ስራው ለጀመረው አዲሱ የእግርኳስ ፌዴሬሽን ይህን መሠል ውይይቶችን በማካሄድ መጀመራችን በቀጣይ ለምናከናውናቸው ስራዎች ጥሩ ግብዓት ይሆኑናል ብለን እናስባለን፡፡ አሁን ላይ ያለው የስፖርታዊ ጨዋነት ችግር በአንድ ጀምበር ምላሽ ሊያገኙ አይችሉም ፤ በቀጣይ በተለያዩ የክልል ክለቦች መካከል ወደ አንዱ ከተማ ሄደን ተዝዋዙረን አንጫወትም የሚሉ ጥያቄዎች መነሳታቸው እስካልቀረ ድረስ አሁን ባለው የውድድር ቅርፅ ይዞ ለመቀጠል ይቸገራል፤ በስፖርት ኮሚሽኑ ይሁንታ ካገኘ እንደ መፍትሔ ሀሳብ ያቀረብነው ወደ ቀደመው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና የውድድር አካሄድ መመለሱ የሚያዋጣ አካሄድ መሆኑን ነው። ” ብለዋል።በመጨረሻም የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ርስቱ ይርዳው በጋራ ሁሉም ባለድርሻ አካል በአንድ ልብ በመስራት መጪውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ጉዞ ብሩህ እናድርግ የሚል መልእክታቸውን አሰተላልፈዋል፡፡ አይይዘው አሁን ያለው የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ቅርፅ ከመቀየር ይልቅ አሁን ባለው የውድድር ቅርጽ ህዝብ ለህዝብ ያለውን ግንኙነት በማጠናከር አብሮነታችንን ለማጎልበት መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡", "passage_id": "5207ce3c0d2aa1508cd92f05e2f79377" }, { "passage": "   አዲስ አባበ ፦ የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባኤ ትናንት አዲስ አበባ ተካሂዷል። በጉባዔው ላይ ከ54አባል አገራት መካከል የ50 አገራት ተወካዮች የተካፈሉ ሲሆን፤ አንድ አባል ደግሞ በቪዲዮ ተከታትለዋል።የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እንዲሁም ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ በክብር እንግድነት ተገኝተው በመድረኩ ንግግር አድርገዋል። ፕሬዚዳንቷ ባደረጉት ንግግርም የሻምበል አበበ ቢቂላ፣ ሻምበል ምሩጽ ይፍጠር፣ ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ እና ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ድሎችን በማንሳት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የድል ተምሳሌት መሆኗን ጠቁመዋል። ለቶኪዮ ኦሊምፒክም ዝግጅቱ\nቀደም ብሎ መጀመሩንና\nየተሻለ ውጤት የሚጠበቅ\nመሆኑን እንዲሁም የአፍሪካ\nኦሊምፒክ ኮሚቴ አፍሪካውያንን\nያሰባሰበ የፓን አፍሪካኒዝም\nማሳያ መሆኑንም ጠቅሰዋል።\nጉባዔው የደንብ እና\nየመመሪያ ማሻሻያ አደርጎ\nተጠናቋል።አዲስ ዘመን ህዳር 28/2013", "passage_id": "1d6419384f1cb1feeaf89d7bc6745c09" } ]
dd2c9c7b55c39e085c52be6d492ca6ec
85f47c0c1d60fc34dafa3b55711aa596
የዓለም ምርጥ ሴት አትሌቶች የመጨረሻ እጩዎች ታወቁ
ከተያዘው ሳምንት ጀምሮ ስሙን የዓለም አትሌቲክስ በሚል የቀየረው የስፖርቱ የበላይ አካል ዓመታዊው የምርጥ አትሌቶች ምርጫውን ሊያካሂድ ቀናት ብቻ ቀርተውታል፡፡ ስፖርት ወዳዱ ህብረተሰብ እንዲሁም የአትሌቶቹ የቅርብ ሰዎች በኢሜይል እንዲሁም በማህበራዊ ድረገጾች በተዘጋጁት ድምጽ መስጫዎች ይገባዋል ለሚሉት አትሌት ይሁንታቸውን ሰጥተዋል፡፡ በእስካሁኑ 25 ከመቶ ድርሻ ባለው የህዝብ ድምጽ እና ባለሙያዎች ባደረጉት ምርጫ መሰረትም የመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ታውቀዋል፡፡በዚህም መሰረት ባለፈው የውድድር ዓመት ብቃታቸው እንዲሁም በቅርቡ በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ባገኙት ውጤት መሰረት ከአምስት ሃገራት አምስት የተለያዩ ሴት አትሌቶች ለመጨረሻው ዙር በቅተዋል፡፡ በመካከለኛ ርቀት ኔዘርላንዳዊቷ ሲፈን ሃሰን ከዓመቱ ምርጥ አትሌቶች መካከል ተገኝታለች፡፡ አትሌቷ በአበረታች ቅመሞች ምክንያት በምርመራ ላይ ከሚገኙት አሰልጣኟ አልቤርቶ ሳላዛር ጋር በተያያዘ በጥርጣሬ ትታይ እንጂ በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በ1ሺ500 እና10ሺ ሜትር አሸናፊ መሆኗ በእጩነት ሊያስመርጣት ችሏል። ይህም ብቻ ሳይሆን የ 1ሺ500 እና 5ሺ ሜትር  የዳይመንድ ሊግ የድርብ ድል ባለቤቷ ሲፈን በማይል ውድድርም 4:12.33 የሆነ የዓለም ክብረወሰንን በሞናኮ አስመዝግባለች። ይህ በአመቱ ያስመዘገበችው ስኬትም አትሌቷን ከዘጠኝ ቀናት በኋላ በሞናኮ በሚኖረው ስነስርዓት የዓለም ምርጥ ሴት አትሌት በመባል የክብሩ ባለቤት እንድትሆን ይረዳታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የአጭር ርቀት ተወዳዳሪዋ ጃማይካዊት አትሌት ሼሊ-አን ፍራዘር-ፕረይሲም በዓመቱ በተካፈለችባቸው ውድድሮች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ለሽልማቱ አሳጭቷታል። አትሌቷ በዶሃው ቻምፒዮና በተካፈለችባቸው የ100 ሜትር እና 4በ400 ሜትር ውድድሮች 10 ሰከንድ ከ71 ማይክሮ ሰከንድ እና 41 ሰከንድ ከ44 ማይክሮ ሰከንድ የሆነ ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ነበረች። የ32 ዓመቷ ፕረይሲ በአሜሪካ አህጉር በሚዘጋጀው ውድድር የ200 ሜትር አሸናፊም ነበረች፡፡ የዓለም ፈጣኗ ሴት አትሌት በአመቱ ከተሳተፈችባቸው አስር ውድድሮች በሰባቱ ቀድማ በመግባት ብርቱ አትሌትነቷን አስመስክራለች፡፡ የሰው ልጅ ማራቶንን ከአንድ ሰዓት በታች መግባት እንደሚችል የሃገራ ልጅ በሙከራ ውድድር ባስመሰከረበት ማግስት የዓለም ሴቶች የማራቶን ክብረወሰንን የሰበረችው ኬንያዊት አትሌት ብርጊድ ኮስጊም ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች መካከል ተገኝታለች፡፡ በቺካጎ ማራቶን ለ16 ዓመታት የቆየውን ክብረወሰን 2:14:04 በሆነ ሰዓት በመግባት የሰባበረችው አትሌቷ የለንደን ማራቶን አሸናፊም ነበረች፡፡ ወጣቷ አትሌት በዓመቱ በተሳተፈችበት የግማሽ ማራቶን ውድድርም 1:04:28 የሆነ ፈጣን ሰዓት አላት። ሌላኛዋ እጩ አሜሪካዊቷ ደሊላ ሙሃመድ በዓመቱ በ400 ሜትር ያሳየችው አቋም ሊያስመርጣት ችሏል፡፡ አትሌቷ በሃገር አቀፍ ቻምፒዮና 52 ሰከንድ ከ20 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ቀዳሚዋ ስትሆን፤ በ400 ሜትር መሰናክል በራሷ የተያዘውን ክብረወሰን 52 ሰከንድ ከ16 ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ብቃቷን አስመስክራለች፡፡ በ4 በ400 ሜትርም በተመሳሳይ የዓለም ቻምፒዮን ናት፡፡ በርዝመት ዝላይ ቬንዙዌላዊቷ ዩሊማር ሮጃስ ለመጨረሻው ዙር መብቃት ችላለች፡፡ አትሌቷ 15.37 ሜትር በመዝለል የዓለም ቻምፒዮን ስትሆን፤ ከዚህ ቀደም የዘለለችው 15.41 ሜትር ደግሞ ከዓለም የምንጊዜም ቀዳሚዎቹ መካከል ሊሰፍርላት ችሏል፡፡ ሮጃስ አህጉር አቀፍ ውድድርን ጨምሮ ከተካፈለችባቸው 12 ውድድሮች ዘጠኝ በሚሆኑት ላይ አሸናፊ መሆኗ ከዓለም ምርጦች ተርታ ያሰልፋታል የሚል ግምት አግኝታለች፡፡አዲስ ዘመን ጥቅም4/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22486
[ { "passage": "ዢ ጂፒንግ በወንዶች፣ አንጌላ መርኬል በሴቶች ቀዳሚነቱን ይዘዋል ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት፤በ2018 የፈረንጆች አመት በተለያዩ መስኮች ተጠቃሽ አለማቀፍ ተጽዕኖ ፈጥረዋል ያላቸውን 75 የዓለማችን ሃያላን ዝርዝር ይፋ ያደረገ ሲሆን በወንዶች የቻይናው ፕሬዚዳንትና የኮሙኒስት ፓርቲ ዋና ጸሃፊ ዢ ጂፒንግ፣ በሴቶች የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርኬል ቀዳሚነቱን ይዘዋል፡፡ላለፉት አራት ተከታታይ አመታት፣ የፎርብስ የአለማችን ቁጥር አንድ ሃያል ሆነው የዘለቁት የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ዘንድሮ ቦታቸውን ለዢ ጂፒንግ አስረክበው፣ ወደ ሁለተኛ ደረጃ ዝቅ ያሉ ሲሆን የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሶስተኛነት ይከተላሉ፡፡የአመቱ የአለማችን ቁጥር አንድ ሃያል ሴት የተባሉት የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርኬል፣ ከአለማችን ሃያላን የአራተኝነት ደረጃን መያዛቸውን የጠቆመው የፎርብስ መግለጫ፤ የአለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ ጄፍ ቤዞስ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡የሮማው ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ፣ የማይክሮሶፍቱ መስራች ቢል ጌትስ፣ የሳዑዲው ልዑል ሞሃመድ ቢን ሳልማን አል ሳኡድ፣ የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲና የጎግል ኩባንያ መስራች ላሪ ፔጅ እንደ ቅደም ተከተላቸው፣ ከስድስተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡በዘንድሮው የፎርብስ የአለማችን ሃያላን ዝርዝር ውስጥ 17 ሰዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የተካተቱ ሲሆን፣ ተራማጅ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የሳዑዲ አረቢያው ልዑል ሞሃመድ ቢን ሳልማን አል ሳኡድ፣ ከእነዚህ አዲስ ገቢዎች አንዱ ናቸው፡፡በአመቱ የአለማችን ሃያላን ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱ ታዋቂ ግለሰቦች መካከል 13ኛ ደረጃን የያዘው የፌስቡኩ መስራች ማርክ ዛከርበርግ፣ 36ኛ ደረጃን የያዙት የሰሜን ኮርያው መሪ ኪም ጁንግ ኡን፣ 66ኛ ደረጃን የያዙት የአፍሪካ ቁጥር አንድ ቢሊየነር ናይጀሪያዊው አሊኮ ዳንጎቴ እና 73ኛ ደረጃን የያዙት የአሸባሪው ቡድን አይሲስ መሪ አቡበከር አል ባግዳዲ ይገኙበታል፡፡ፎርብስ የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪነት፣ ተሰሚነት፣ የሃብት መጠን፣ የስኬት ደረጃና የመሳሰሉትን መስፈርቶች በመጠቀም ከገመገማቸውና በዝርዝሩ ውስጥ ካካተታቸው የአመቱ ሃያላን መካከል የአገራት መሪዎች፣ የኩባንያ ባለቤቶችና የስራ ሃላፊዎች፣ የተቋማትና ቡድኖች መሪዎች ወዘተ ይገኙበታል፡፡", "passage_id": "37149cec482d4edc067cef4f2d38a056" }, { "passage": "በስፖርቱ ዓለም በተለይም በእግር ኳስና አትሌቲክስ ብዙም የማትታወቀው ህንድ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተለያዩ የአትሌቲክስ የጎዳና ላይ ውድድሮችን እያስተናገደች ትገኛለች። በዚህም በመዲናዋ በየዓመቱ ከምታዘጋጀው የዴልሂ ማራቶንና ግማሽ ማራቶን ውድድር አንስቶ በሌሎች የጎዳና ላይ ውድድሮችም ከዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ደረጃ የተሰጣቸው ፉክክሮችን ለማስተናገድ ችላለች። የፊታችን እሁድም የነሐስ ደረጃ የተሰጠውን የካልካታ ሃያ አምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ታካሂዳለች።\nበዚህ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአሸናፊነት ግምት ያገኙ ሲሆን፤ በተለይም በሴቶች መካከል በሚካሄደው ውድድር የአምናዋ አሸናፊ አትሌት ደጊቱ አዝመራው ዳግም ለአሸናፊነት ታጭታለች። ባለፈው ዓመት ይህች የአስራ ስምንት ዓመት ኢትዮጵያዊት አትሌት በመጀመሪያ ዓለም አቀፍ ውድድሯ የቦታውን ክብረወሰን 1፡26፡01 በሆነ ሰዓት በማሻሻል ጭምር አሸንፋ በርካቶችን እንዳስደ መመች አይ ኤኤ ኤፍ በድረ ገፁ አስፍሮታል።\nአትሌት ደጊቱ በ2018 የውድድር ዓመት በጎዳና ላይ ሌሎች ውድድሮችን አድርጋም ውጤታማ ነበረች። ባለፈው የካቲት ወር በራክ ግማሽ ማራቶን ተወዳድራ የራሷን ምርጥ ሰዓት ወደ 1፡06፡47 አውርዳለች። ከዚህም በኋላ በጃፓን ጊፉ ግማሽ ማራቶን ማሸነፍ ችላለች። ይህም በዘንድሮው ውድድር ለአሸናፊነት እንድትጠበቅ አድርጓታል። ይሁን እንጂ ከኬንያዊቷ ጠንካራ አትሌት ፍሎሬንስ ኪፕላጋት የሚገጥማት ፈተና ቀላል እንደ ማይሆን ይታመናል።\nእኤአ 2009 ላይ በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና እንዲሁም 2010 ላይ በዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያዎችን ማጥለቅ የቻለችው ኪፕላጋት በጎዳና ላይ ውድድሮች በርካታ ልምዶችን ከማካበቷ ባሻገር የቀድሞ የዓለም የግማሽ ማራቶን ባለ ክብረወሰን እንደነበረች ይታወሳል። ኪፕላጋት አሁን ሰላሳ አንደኛ ዓመቷ ላይ የምትገኝ ቢሆንም፤ ከወጣቷ ኢትዮጵያዊት ጋር ለመፎካከርና አሸናፊ ለመሆን የተሻለ እንጂ ያነሰ እድል የላትም።\nኪፕላጋት ባለፈው ዓመት በዚሁ በካልካታ ሃያ አምስት ኪሎ ሜትር ውድድር ላይ ትሳተፋለች ተብሎ ቢጠበቅም ቀደም ብሎ ቺካጎ ማራቶን ላይ በገጠማት ጉዳት ሳቢያ ለውድድሩ ብቁ ሆና መገኘት አልቻለችም። ዘንድሮ ግን ያለፈውንም ቁጭቷን ለመወጣት ወደ ህንዷ የኢንዱስትሪ ከተማ እንደምታቀና ታውቋል። በእርግጥ ኪፕላጋት ከዚሁ ከጉዳት ጋር በተያያዘ ከወር በፊት በቺካጎ ማራቶን አራተኛ ደረጃን ይዛ እስካጠናቀቀችበት ውድድር ለዓመት ያህል ከፉክክር ርቃ ቆይታለች። ኪፕላጋት በካልካታ ውድድር ላይ ስትሳተፍ የዘንድሮው የመጀመሪያዋ ቢሆንም ህንድ አገር በሚካሄዱ ውድድሮች እንግዳ አይደለችም። ከዚህ ቀደም በዴልሂ ግማሽ ማራቶን ሁለት ጊዜ ማሸነፏ ይታወሳል። በውድድሩ ሱቱሜ አሰፋ የተባለች ኢትዮጵያ ዊት እንዲሁም ፌሉና ማታንጋ የተባለች ታንዛኒያዊት አትሌት ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።\nበተመሳሳይ ውድድር በወንዶች መካከል የቦታው ብቻም ሳይሆን በህንድ አገር ከተሮጡ ፈጣን ሰዓቶች ሁሉ ክብረወሰን ሊሆን የሚችል ሰዓት ይመዘገባል ተብሎ ይጠበቃል። የቦታው ክብረወሰን ባለፈው ዓመት በጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 1፡13፡48 ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል። ያለፈው ዓመት ውድድር ቀነኒሳን ጨምሮ በሴቶችም ውድድር ጠንካራና ስመ ጥር አትሌቶች ሲሳተፉ የመጀመሪያው እንደነበር ይታወቃል።\nዘንድሮ በወንዶች መካከል በሚካሄደው ውድድር ለህንድ አትሌቲክስ አፍቃሪዎች አዲስ ያልሆነው ኢትዮጵያዊው አትሌት ብርሃኑ ለገሰ ለአሸናፊነት ይጠበቃል። ብርሃኑ ሁለት ጊዜ በዴልሂ ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮን ከመሆኑ ባሻገር በባንግሎር አስር ኪሎ ሜትርና ሌሎች ውድድሮች ላይ በመሳተፍ በህንድ ታዋቂ ነው።\nብርሃኑ በውድድሩ ከኬንያዊው ኤሪክ ኪፕቱናይ ብርቱ ፉክክር የሚጠብቀው ሲሆን፤ የኤርትራ፣ ታንዛኒያ እንዲሁም ሌሎች የኢትዮጵያና ኬንያ አትሌቶች ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተለይም ኬንያዊው ኪፕቱናይ በ2018 የውድድር ዓመት ባለፈው የበርሊን ግማሽ ማራቶን ያሰመዘገበው 58፡42 ሰዓት በውድድር ዓመቱ ሦስተኛው ፈጣን ሰዓት መሆኑ ትኩረት እንዲሰጠው አድርጓል። የታንዛኒያ ባለክብረወሰን ኦገስቲኖ ሱሌ ባለፈው ዓመት በዚህ ውድድር ሦስተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ የሚታወስ ሲሆን ዘንድሮ ጠንካራ ተፎካካሪ እንደሚሆን ይጠበቃል።", "passage_id": "d7cafb48c3406b2cf8ddc51b81314427" }, { "passage": "ስኬታማ ከሆኑት የሴት እግር ኳስ ቡድኖች መካከል ቀዳሚዎቹ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች\n\nውድድሩ በ1991 (እአአ) ከጀመረ ወዲህ በማስታወቂያ፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ነገሮች ጉልህ መሻሻልን በማሳየት የወንዶቹን ያህል እንኳን ባይሆንም ያለውን ሰሪ ልዩነት በተወሰነ ደረጃ በማጥበብ ይካሄዳል። \n\nየሚከተሉት ስድስት ጉዳዮች የሴቶች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ያሳየውን ዕድገት ያሳያሉ። \n\nተሳታፊዎችና ተመልካቾች \n\nከአራት ዓመታት በፊት ካናዳ ውስጥ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ላይ የተደረጉትን 52 ግጥሚያዎች 1.35 ሚሊዮን ሰዎች ተመልክተውታል። \n\nየዓለም እግር ኳስ የበላይ አካል የሆነው ፊፋ፤ ፈረንሳይ የምታስተናግደው የዚህ ዓመቱ የሴቶች እግር ኳስ የዓለም ዋንጫ ውድድርን ከባለፈው ጋር ተመሳሳይ አሊያም የበለጠ ቁጥር ያለው ሰው ይመለከተዋል ብሎ ይጠብቃል። ጨምሮም በቴሌቪዥን ውድድሩን የሚመለከተው ሰው ቁጥር ከባለፈው የዓለም ዋንጫ ከፍ እንደሚልም አመልክቷል። \n\n• «የኔ ትውልድ ታሪክ እንደሚሠራ እምነት አለኝ» ሎዛ አበራ \n\nይህ የሴቶች የዓለም ዋንጫ በ1995 (እአአ) ኖርዌይ ውስጥ ሲካሄድ እያንዳንዱን ጨዋታ በአማካይ 4500 ሰዎች ብቻ ነበር የተመለከቱት። በአጠቃላይ ውድድሩን የተመለከቱት ሰዎች ደግሞ ከ112 ሺህ ያህል ብቻ ነበሩ። \n\nአዲሱ የኔዘርላንድስ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ማሊያ\n\nአመቺና ተመራጭ የስፖርት አልባሳት \n\nበዚህ ዓመቱ የሴቶች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ላይ ከሌላው ጊዜ በተለየ ተጫዋቾቹ ለወንዶች የተዘጋጀ የስፖርት ትጥቅን ሳይሆን ለሴቶች ተብለው የተዘጋጁ ትጥቆችን ይለብሳሉ። \n\nለዚህም በውድድሩ ከሚሳተፉት 24 ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የሦስተ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊዋን አሜሪካንን፣ አስተናጋጇን ፈረንሳይን፣ የአውሮፓ ሻምፒዮናን ኔዘርላንድስ እና ብራዚልን ጨምሮ 14 ቡድኖችን ስፖንሰር ያደረገው የስፖርት ትጥቆች አምራች ድርጅቱ ናይኪ ነው። \n\n • ''ብሔርተኝነት'' እያጠላበት ያለው እግር ኳስ \n\nየድርጅቱ የምርምርና የዲዛይን ቡድን የሴት እግር ኳስ ተጫዋቾች ፍላጎትን ከግምት በማስገባት ረጅም ጸጉር ላላቸው በቀላሉ የሚለበስና የሚወልቅ ማሊያዎች እንዲሁም ሰውነትን የማያጋልጡ ነገር ግን እንቀስቃሴን የማይገድቡ ቁምጣዎችን አዘጋጅቷል። \n\nየኔዘርላንድስ ቡድን ማሊያም የሃገሪቱ ወንድ እግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾች ደረት ላይ ይደረግ የነበረውን የወንድ አንበሳ ምስል በመቀየር ለሴቶቹ ምስሉ የሴት አንበሳ እንዲሆን ተደርጓል። \n\nእራሷን ከዓለም ዋንጫ ያገለለችው አዳ ሄገርበርግ\n\nዝቅተኛ ክፍያ \n\nየሴቶች እግር ኳስ ውድድር አሁንም ድረስ በገቢና በክፍያ በኩል ከወንዶቹ አቻቸው በእጅጉ ዝቅ ያለ ነው። ከሴቶች እግር ኳስ ተጫዋቾች መካከል ከፍተኛውን ክፍያ የምታገኘው የኖርዌይ ዜጋዋ አዳ ሄገርበርግ ስትሆን በዓመት የሚከፈላት 450 ሺህ ዶላር ነው። \n\nይህም ከአርጀንቲናዊው አጥቂ ሌዮኔል ሜሲ ጋር ሲነጻጸር በ325 እጥፍ ያነሰ መሆኑን ፍራንስ ፉትቦል የተባለው መጽሔት ያካሄደው ዓመታዊ ጥናት ያመለክታል። \n\nየዚህ ዓመቱ የሴቶች የዓለም ዋንጫ ውድድር 30 ሚኒዮን ዶላር በሽልማት መልክ ለውድድሩ ተሳታፊዎች ይሰጣል። ይህም ቀደም ባለው ውድድር ላይ ከቀረበው እጥፍ ሲሆን በውድድሩ ታሪክም ከፍተኛው ነው። \n\n• ሞ ሳላህ ለሊቨርፑል መፈረሙ በከተማዋ ሙስሊም ጠልነት ቀነሰ \n\nነገር ግን ለውድድሩ አሸናፊ ብድን 4 ሚሊዮን ዶላር የሚሰጥ ሲሆን ይህ በወንዶቹ ውድድር ላይ ከ16ቱ የዙር ፉክክር የሚሰናበቱ ቡድኖች ከሚያገኙት ገንዘብ ግማሹ ነው። \n\nይህ በወንዶችና በሴት እግር ኳስ ተጫዋቾች መካከል ያለው ሰፊ ልዩነት ኖርዌያዊቷ ሄገርበርግ ከዓለም ዋንጫ አራሷን እንድታገል አድርጓታል። ተጫዋቿ... ", "passage_id": "817e5fc5a1ef24ecfd0860c534f5d8f2" }, { "passage": "በዘንድሮው የፎርብስ የዓለማችን ከፍተኛ ተከፋይ 10 ተዋንያን ውስጥ ሁለት ሴቶች ይገኙበታል\n\nየዓለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ተዋናዮች ዝርዝር ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ስሟ የሰፈረ ሲሆን በአጠቃላይ አሥር ተዋንያን ዝርዝር ውስጥ ደግሞ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።\n\n• ኢንተርኔትን የሚሾፍረው የወሲብ ፊልም ይሆን?\n\nየ34 ዓመቷ ተዋናይት ስካርሌት ጆሃንሰን ያስመዘገበችው 56 ሚሊን ዶላር ሰባተኛ ደረጃ ከያዘው ወንድ ተዋናይ አዳም ሳንድለር ጋር ይስተካከላል።\n\nበ'ሞደርን ፋሚሊ' ተከታታይ ፊልም ላይ የምትተውነው ሶፊያ ቨርጋራ ደግሞ ከአሥሩ የዓለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ተዋናያን ሁለተኛዋ ሴት ሆናለች። \n\nባላፉት 12 ወራት 89.4 ሚሊየን ዶላር በማስመዝገብ አሜሪካዊው ተዋናይ ድዋይን ጆንሰን [ዘ ሮክ] ከፍተኛ ተከፋይ ተዋናይ በመሆን ቀዳሚነቱን ይዟል።\n\nከ1-10ኛ ደረጃ የያዙት ተዋንያን በዚህ ዓመት ከ20 ሚሊየን ዶላር በላይ ያስመዘገቡ ሲሆን ባለፈው ዓመት የመጀመሪያዎቹን ሁለት ደረጃዎች የተቆናጠጡት ስካርሌት ጆሃንሰንና አንጀሊና ጆሊ ብቻ ነበሩ።\n\nሶፊያ ቬርጋራ፣ ጀኔፈር አኒስተን እና ማርጎት ሮቤ [ ከግራ ወደ ቀኝ]\n\nባለፈው ዓመት አንጀሊና ጆሊ 28 ሚሊየን ዶላር ብታስመዘግብም በዘንድሮው አሥሮች ዝርዝር ውስጥ መግባት አልቻለችም።\n\nአንጀሊና በአሁኑ ሰዓት \"ሚስትረስ ኦፍ ኢቪል\" እና \"ዘ ዋን ኤንድ ኦንሊ ኢቫን\" የተሰኙ ሁለት አዳዲስ ፊልሞች ላይ እየተወነችና እያዘጋጀት ትገኛለች። \n\nበዚህ ዓመት ዝርዝር ውስጥ ካልተካተቱ ተዋንያን መካከል ሚላ ኩኒስ፣ ጁሊያ ሮበርት፣ ሜሊሳ ምካቲይ እና ጋል ጋዶት ይገኙበታል።\n\n• የምርጥ ተዋናይቷን ኦስካር ሽልማት የሰረቀው በቁጥጥር ስር ዋለ\n\n• የኢትዮጵያ ፊልም ወዲያና ወዲህ\n\nበዘንድሮው የከፍተኛ ተካፋይ ተዋንያን ዝርዝር፤ ከወንድ ተዋንያን ዝርዝር በስተቀር በሴቶቹ ዘርፍ ብዙም ስብጥር አልታየም፤ ሶፊያ ቬርጋራ ኮሎምቢያዊ አሜሪካዊት ስትሆን በዝርዝሩ ውስጥ ጥቁር አሜሪካዊ ተዋንያን አልነበሩም።\n\nየዘንድሮ የዓለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ሴት ተዋንያን\n\n1. ስካርሌት ጆሀንሰን [56 ሚሊየን ዶላር]\n\n2. ሶፊያ ቬርጋራ [44.1 ሚሊየን ዶላር]\n\n3. ሪስ ዊዘርስፑን [35 ሚሊየን ዶላር]\n\n4. ኒኮል ኪድማን [34 ሚሊየን ዶላር] \n\n5. ጀኔፈር አኒስተን [28 ሚሊየን ዶላር]\n\n6. ካሌይ ኩኮ [25 ሚሊየን ዶላር]\n\n7. ኤልዛቤት ሞስ [24 ሚሊየን ዶላር]\n\n8. ማርጋሬት ሮቤ [23.5 ሚሊየን ዶላር]\n\n9. ቻርሊዝ ቴሮን [23 ሚሊየን ዶላር]\n\n10. ኤለን ፖምፔዎ [22 ሚሊየን ዶላር]\n\nአሜሪካዊው ተዋናይ ድዋይን ጆንሰን (ዘ ሮክ)\n\nፎርብስ የዓለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ወንዶች ተዋናይ ዝርዝርም ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ይፋ አድርጓል።\n\nዘ ሮክ በሚለው ቅፅል ስሙ የሚታወቀው አሜሪካዊው ተዋናይና ዳሬክተር ድዋይን ጆንሰን ምንም እንኳን ባለፈው ዓመት አስመዝግቦት ከነበረው 119 ሚሊየን ዶላር ዝቅ ቢልም፤ ከነበረበት ሁለተኛ ደረጃ ከፍ ብሎ አንደኛነትን ይዟል።\n\n• ዕውቁ አሜሪካዊው ተዋናይ ዘ ሮክ በሚስጢር ተሞሸረ\n\nባለፈው ዓመት በፎርብስ ዝርዝር ውስጥ አንደኛ ሆኖ የተመዘገበው ጆርጅ ክሉኒ ግን በዘንድሮው አሥሮቹ ዝርዝር ውስጥ መግባት አልቻለም።\n\nምክንያቱም ባለፈው ዓመት አስመዝግቦት ለነበረው ከፍተኛ ገንዘብ አስተዋፅኦ ያደረገለት እና 1 ቢሊየን ዶላር የሚገመተው የአልኮል ማምረቻ ድርጅቱ በመሸጡ ገቢው በማሽቆልቆሉ ነው። \n\nበዝርዝሩ፤ ሁሉም ዝነኞች ከማስታወቂያ እና ትወና በተጨማሪ ከሌሎች የገቢ ምንጮች የሚያገኙትንም ገቢ ያማከለ ነበር። \n\nበዚህ ዓመት የፎርብስ ከፍተኛ ተከፋይ ተዋንያን ዝርዝር ሁለተኛ ደረጃን የያዘው ክሪስ ሄመንስዎርዝ ሲሆን 76.4 ሚሊየን... ", "passage_id": "63065916c0382f7757745b605a5e83ad" }, { "passage": "በአዲሱ የፈረንጆች ዓመት የመጀመሪያው ወር ከሚካሄዱ የጎዳና ላይ ሩጫዎች መካከል አንዱ የሆነውና ‹‹ሜጀር›› ከሚባሉት ውድድሮች የሚመደበው የዱባይ ማራቶን ሊካሄድ ቀናት ብቻ ቀርተውታል፡፡ እንደተለመደው በሞቀና በደመቀ ሁኔታ ውድድሩ ሊካሄድም በዓለም ዝነኛ የሆኑ አትሌቶች ተሳታፊነታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በሁለቱም ጾታ የማራቶን ውድድር ቀዳሚ በመሆን ያጠናቀቁትና ዓለም አቀፉ የጎዳና ላይ ውድድሮች ማህበር የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች በማለት የመረጣቸው አትሌቶችም በዱባይ ተሳታፊ ይሆናሉ:: ይህም የስፖርት ቤተሰቡን ልብ ወደ ውድድሩ አስቀድሞ እንዲሳብ ያደረገና ፉክክሩንም በጉጉት የሚጠበቅ አድርጎታል፡፡ በዱባይ ልዑል ሼክ ሃምዳን ቢን ሞሃመድ ቢን ረሺድ አል መክቱም ድጋፍ የሚደረግለትና በዱባይ ስፖርት ምክር ቤት የሚመራ ውድድር ነው:: በማራቶን፣ 10ኪሎ ሜትር እና 4 ኪሎ ሜትር የሚካሄደው ውድድሩ፤ ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ከሚያስገኙ የጎዳና ላይ ሩጫዎች መካከል ይጠቀሳል፡፡ ከቀናት በኋላ በሚካሄደው ውድድር ላይ ደግሞ 30ሺ የሚሆኑ አትሌቶች ተሳታፊዎች እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡ እ.አ.አ ከ2000 በመካከለኛዋ ምሥራቅ ከበርቴ ሀገር መካሄድ የጀመረው የዱባይ ማራቶን በአጭር ጊዜ ትልቅ ቦታ መድረስ የቻለ ውድድር ነው፡፡ በዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ የተሰጠው ውድድሩ በቦታው የአየር ሁኔታና የቦታ አቀማመጡ ምክንያት ፈጣን ሰዓት ለማስመዝገብ የሚረዳ መሆኑ የበርካታ አትሌቶች ምርጫ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ በተለይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ደግሞ ከሚመርጧቸውና ውጤታማ ከሆኑባቸው መድረኮች መካከል ተጠቃሽ ነው፡፡ እ.አ.አ በ2005 በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊ ከሆኑ አንስቶም ድሉ ከጥቂት ጊዜያት በቀር ከእጃቸው ሊወጣ አልቻለም፡፡ ባለፈው ዓመት በተካሄደው 20ኛው የዱባይ ማራቶን በወንዶች በኩል አንድ ኬንያዊ አትሌት ብቻ ጣልቃ በማስገባት ከአንድ እስከ ዘጠኝ ያለውን ደረጃ በመያዝ ነበር ያጠናቀቁት፡፡ በሴቶች በኩል ደግሞ የአንደኝነት ስፍራው በኬንያዊቷ አትሌት ቢያዝም ከሁለተኛ እስከ ሦስተኛ ባለው ኢትዮጵያውያን ተከታትለው በመግባት በቦታው ያላቸውን የበላይነት አሳይተዋል፡፡ የቦታው ክብረወሰን የተመዘገበውም በዚሁ ዓመት ሲሆን፤ ጌትነት ዋለ 2:03:34 ሲያስመዘግብ ኬንያዊቷ ሩት ቼፕጌቲች ደግሞ 2:17:08 በሆነ ሰዓት ነበር የገባችው፡፡ በዚህ ውድድር ደግሞ በተለይ በርቀቱ ታዋቂ የሆኑ አፍሪካውያን አትሌቶች በዚህ ሜጀር ውድድር ላይ መገናኘትም ውድድሩን ፈታኝ ያደርገዋል የሚል ቅድመ ግምት ባገኘው በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡ በውድድሩ ላይ በወንዶች ምድብ ተሳታፊ ከሚሆኑት አትሌቶች መካከል ፈጣን ሰዓት ያለው ሰለሞን ዴክሲሳ፤ 2:04:40 የሆነ ሰዓት አለው፡፡ የ25 ዓመቱ አትሌት ከአምስት ዓመታት በፊት በጎዳና ላይ ውድድር የታየው በሳንዲያጎ ማራቶን ሲሆን፤ በአሸናፊነት ያጠናቀቀበት ሰዓት ደግሞ 60:12 ነው፡፡ ሁለት ዓመት ባልሞላ፤ ጊዜ ውስጥ ወደ ማራቶን በመግባት የሮተርዳም ማራቶንን በሁለተኝነት ሮጦ ለመጨረስ 60:12 ፈጅቶበታል፡፡ እ.አ.አ በ2018ቱ የሙምባይ ማራቶን እንዲሁም በቅርቡ በተካሄደው የሃምቡርግ ማራቶን ላይም ድልን መቀዳጀት የቻለ ብርቱ ወጣት አትሌት ነው፡፡ የተጠናቀቀው የፈረንጆቹ ዓመትም ለሰለሞን መልካም የሚባል ሲሆን፤ በአምስተርዳም ማራቶን 2:04:40 የሆነ የግሉን ፈጣን ሰዓት አስመዝግቧል፤ በዱባይ ማራቶን ተሳትፎውም በአንድ ደቂቃ በመዘግየቱ የሀገሩን ልጅ በመከተል ሁለተኛ ነበር የሆነው፡፡ሌላኛው የርቀቱ የፈጣን ሰዓት ባለቤትና የሰለሞን ተፎካካሪ ኢትዮጵያዊው ሰይፉ ቱራ 2:04:44 የሆነ ሰዓት አለው፡፡ የ22 ዓመቱ ሰይፉ በዱባይ ማራቶን ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈው እአአ 2018 ሲሆን፤ ውድድሩን በሰባተኝነት ሲያጠናቅቅ ያስመዘገበው ሰዓት 2:04:44 ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ በተካፈለባቸው የሚላን እና የሻንጋይ ማራቶኖች እንዲሁም የቦነስ አይረስ ግማሽ ማራቶን ውድድሮች ተካፍሎ ውጤት በማስመዝገብ የውድድር ልምድ ማግኘት የቻለ ወጣት አትሌት ነው፡፡ በሴቶች ምድብ ደግሞ ፈጣኗ ወርቅነሽ ደገፋ የምትመራ ሲሆን፤ የረጅም ጊዜ የቦታውን ተሳታፊነት ልምዷን ተጠቅማ በአሸናፊነት ታጠናቅቃለች በሚል ትጠበቃለች፡፡ የ29 ዓመቷ ወርቅነሽ በዱባይ ለመጀመሪያ ጊዜ የሮጠችው እ.አ.አ በ2017 ሲሆን፤ በቀጣዩ ዓመት አራተኛ ደረጃን በመያዝ 2:20 የሆነ የግሏን ፈጣን ሰዓት አስመዝግባለች፡፡ በተጠናቀቀው ዓመት በኬንያዊቷ አትሌት ተቀድማ ሁለተኛ ብትሆንም ያስመዘገበችው ሰዓት ግን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከገቡባቸው በ15 ሰከንዶች የፈጠነ 2:17:41 ነበር፡፡ በሴቶች ማራቶን ውድድር ታሪክ ከተመዘገቡ ፈጣን ሰዓቶች አምስተኛ ደረጃ ላይ የሚቀመጥ ነው፡፡ የዱባይ ማራቶን ዳይሬክተር የሆኑት ፒተር ኮኔርተን ውድድሩን አስመልክቶ ‹‹ከተማዋ በዓለም ፈጣን የሆነውን ውድድር ለማስተናገድ በዝግጅት ላይ ትገኛለች፡፡ አትሌቶችም በዓመቱ የመጀመሪያ በሆነው ሜጀር ውድድር ላይ ለመሳተፍ እየተዘጋጁ ነው፡፡ የአየር ሁኔታውና የመሮጫ ጎዳናውም ቢሆን አትሌቶች ፈጣን ሰዓት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችላቸው ነው›› ብለዋል፡፡ አዲስ ዘመን\nጥር 11 /2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "6d4ca420b65b69787b0a4eca459fe539" } ]
0b957c344747e02c7e37aa257da3ec5c
6d2cfade0e42aee16171d154944096b8
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በታላቅ የስኬት ጎዳና
ኢትዮጵያ በአትሌቲክሱ ዓለም በተለይም በረጅም ርቀት ውድድሮች ገናና ስም በማትረፍ ትታወቃለች።በረጅም ርቀት ውድድሮች ቁጥር ስፍር የሌላቸው ብርቅዬ አትሌቶቿ ከሰሩት ዘመን የማይሽረው ታሪክ ጎን ለጎን በአትሌቲክሱ ዓለም አንድ የሚጠቀስ ታላቅ ስኬትም እያስመዘገበች ትገኛለች።ይህ ስኬትም በጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ መስራችነት የተጀመረው ‹‹ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ›› የተሰኘው ታላቅ የጎዳና ላይ ውድድር ነው።ኢትዮጵያ ስፖርትን እንደቱሪዝም በመጠቀም ረገድ ብዙ ባልተጓዘችበት ዘመን ከሁለት አሥርት ዓመታት በፊት የተጠነሰሰው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ከስፖርታዊ ኩነቱ አይሎ የስፖርት ቱሪዝም ጥያቄን እስከ መመለስ ደርሷል።ከዓለም ምርጥ አሥር ተወዳጅና ሳቢ የጎዳና ላይ ሩጫዎች መካከል አንዱ የሆነው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በተወዳጅነት እንደዘለቀ ከሚያገኘው ገቢ ለሰብዓዊ እርዳታ እያዋለ ኢትዮጵያን በበጎ እያስጠራ ይገኛል።ይህም የዓለም አትሌቲክስ አፍቃሪዎችን ከየአቅጣጫው እየሳበ የተሳታፊዎቹን ቁጥር ከዓመት ዓመት እንዲመነደግ አስችሎታል።ከወር በፊትም “በሌትስ ዱ ዚስ” የሚታገዘውና በእውቁ የሩጫ መጽሔት “ረነርስ ወርልድ” የሚቀርበው “ዘ ቻሌንጅስ አዋርድ” የተሰኘ ውድድር በጎዳና ላይ ውድድር ዝግጅት ዘርፍ ትልቁን ዓለም አቀፍ ሽልማት ማሸነፍ ችሏል።ይህም ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን ከዓለማችን ስኬታማ የውድድር አዘጋጆች ጎራ ሲያሰልፈው የሀገራችንን ስም በበጎ የሚያስነሳ ሌላ ትልቅ ብሔራዊ ሀብት አድርጎታል።ደማቁና ተናፋቂው ዓመታዊ የአስር ኪሎ ሜትር ውድድርም ነገ ለ19 ጊዜ 45ሺ ተሳታፊዎችን ሊያወዳድር ዝግጅቱን አጠናቆ እየተጠባበቀ ይገኛል።ይህንን በማስመልከትም አዲስ ዘመን ቅዳሜ በውድድሩ ዋዜማ ላይ ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ አየለ ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ የሚከተለውን ይመስላል፡፡አዲስ ዘመን፡- ነገ በጉጉት ስለሚጠበቀው ውድድር ምን ማለት ይቻላል?አቶ ኤርሚያስ፡- ይህንን ውድድር በ1993 ዓም የጀመርነው በ10ሺ ሰው ብቻ ነበር፤ በየዓመቱ ሳይቋረጥ ሲካሄድ ቆይቶም ዘንድሮ ለ19ኛ ጊዜ ሲካሄድ 45ሺ ሰዎችን በማሳተፍ ነው።በእርግጥ ፍላጎቱ ከዚያም የበለጠ ነው፤ ነገር ግን ለውድድሩ ጥራት በማሰብ እንዲሁም ከመወዳደሪያ ቦታ ጥበት ጋር በተያያዘ ቁጥሩን ገድበነዋል።ሩጫው እንደሚታወቀው ሁሉንም የሚያሳትፍ በመሆኑ ተሳታፊዎችን የሚያዝናና የሚያስደስት ይሆናል፡፡አዲስ ዘመን፡- ዘንድሮ ካለፉት 19 ዓመታት የተለየ ምን አዲስ ነገር እንጠብቅ? አቶ ኤርሚያስ፡- ቁጥሩ ላይ ጭማሪ አድርገናል፣ አብዛኛው ተሳታፊ ርቀቱን የሚጨርሰው በእርምጃ ከመሆኑ ጋር ተያይዞም ከአንድ ሰዓት በታች የሚገቡ ሯጮችን ቀድመው እንዲነሱ የሚያደርግ የተለየ ቀለም ያለው ከነቴራ (አረንጓዴ ማዕበል) እንዲለብሱ በማድረግ ላለፉት ዓመታት ተሞክሯል፤ ነገር ግን እንደሚፈለገው አልሆነልንም ነበር።በመሆኑም በሰዓት በመከፋፈልና ተሳታፊዎች እንደ ከነቴራቸው ቀለም በየመካከሉ አካላዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ በመቆየት ከጥቁር አንበሳ አካባቢ የሚጀምሩትን የአትሌቶችን እና ሌሎቹን በመለያየት የምናካሂድ ይሆናል።እንደተለመደው ውድድሩ ስድስት ሳምንት ሲቀረው ጀምሮ ተሳታፊው ለሩጫው ዝግጅት እንዲያደርግ ቅስቀሳ ስናደርግ ነበር።የመጀመሪያው ሳምንት ዱብ ዱብ ሲሆን፤ ተሳታፊዎች እንቅስቃሴ ከጀመሩ በኋላ ጤናቸውን እንዲመለከቱ ለማድረግ ሁለተኛውን ሳምንት ጤና ብለንዋል።እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሄራዊ ቡድን አረንጓዴ ጎርፍ በሚል ስያሜ ነው የሚጠራው፤ ነገር ግን ጎርፍ ከመሆኑ አስቀድሞ ምንጭ ነውና እኛም የአዳዲስ ስፖርተኞች መታያ እንደመሆናችን ምንጭ ስንል ሰይመነዋል።በነገራችን ላይ ከዚህ ቀደም ለመሳተፍ የሚፈልጉ አትሌቶች ሁሉ ጥያቄ ያቀርቡ ነበር አሁን ግን ይህ እንዳይፈጠር አስቀድመን የማጣሪያ ውድድር አዘጋጅተን ነበር።ቀጣዩን ሳምንት የበጎ ፈቃደኞች ሳምንት ያልነው ሲሆን ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን ልምድ የማካፈል ስራ አከናውነናል።አምስተኛው ሳምንት ደግሞ የጽዳት በማድረግ ውድድሩ የሚካሄድበትን ስፍራ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ከመነሻ እስከ መድረሻ ያለውን አጽድተናል። የመጨረሻውን ሳምንትም የስፖርት ኤክስፖ ሆኖ ነው ያለፈው።አዲስ ዘመን፡- ሌሎች ከሩጫው ጋር የተያያዙ መርሐ ግብሮችስ ይኖራሉ?አቶ ኤርሚያስ፡- በተለየ የምንሰራው የበጎ አድራጎት ስራ ላይ የመሮጫ ከነቴራዎቹን ለበጎ አድራጎት ለማዋል በ900ብር እንዲሸጥ የማድረግ አንዱ መርሐ ግብር ነው።በዚህም ዘንድሮ በዋግህምራ ዞን አንድ ትምህርት ቤት ለማስገንባት የሚውል ይሆናል። ዛሬ የሚካሄደው የህጻናት ሩጫ እና ምሽት ላይ ደግሞ ከውጪ ሀገራት የሚመጡ ተሳታፊዎቻችንን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት አቀባበል የምናደርግበትም መርሐ ግብር አለን፡፡አዲስ ዘመን፡- ታላቁ ሩጫ ከሩጫነቱ በዘለለ የሃገር ገጽታ መገንቢያም ሆኗልና በዚህ የረጅም ጊዜ ቆይታው እንደሃገርም ሆነ እንደ ተቋም ያሳካችሁት ምንድነው?አቶ ኤርሚያስ፡- ያሳካነው በርካታ ቢሆንም በዋናነት ግን አራት ጉዳዮችን ማንሳት ይቻላል፤ የመጀመሪያው ከዓመት ዓመት የሃገራችንን በጎ ገጽታ ማሳየት መቻላችን ነው።ወቅታዊ ሁኔታዎች ባይፈትኑን ደግሞ እጅግ በርካታ የውጪ ሃገራት ዜጎች በሩጫው ለመካፈል ወደ እዚህ ይመጣሉ።ያልተቋረጠ የውጪ ሃገራት መገናኛ ብዙሃን ሽፋን ማግኘትም ለሃገሪቷ መልካም ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ሚና አለው።ሁለተኛው ስኬት በሃገር ውስጥ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ እንዲለመድ አድርገናል።ሌላኛው ለአትሌቶች ምቹ የመታያ መድረክ መሆናችን ነው።ማናጀሮች አትሌቶችን ለመመልከት የሚታደሙ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በአብዛኛው ከአንድ እስከ አስር የሚወጡት አትሌቶች ማናጀር የማግኘት እድላቸው የሰፋ ነው።ይህም ለአትሌቶች ምቹ መድረክ ይፈጥራል።ሌላኛው ጉዳይ ደግሞ የበጎ አድራጎት ስራ ሲሆን፤ ባለፉት ስድስትና አምስት ዓመታት ብቻ ያሰባሰብነው ገንዘብ ወደ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ነው፤ በዚህም በርካታ ድርጅቶችን መርዳት ችለናል፡፡አዲስ ዘመን፡- ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ እንደ ሌሎች ሃገራት ውድድሮች በዓለም አትሌቲክ ደረጃ ተሰጥቶት ለምን አይካሄድም የሚለውም የብዙዎች ጥያቄ ነውና ውድድሩ ደረጃ እንዲያገኝ ያሰባችሁት ነገር አለ?አቶ ኤርሚያስ፡- እኛ የኤይምስ አባል ነን ይህም የዓለም አትሌቲክስ ከሚሰጠው ደረጃ በእኩል መቀመጥ የሚችል ነው።እንደ እኛ ሁሉ ከ400 በላይ የሚሆኑ ሩጫዎችም የዚህ አባል ሲሆኑ የእኛ የጎዳና ላይ ሩጫም ከእነዚህ መካከል አንዱና ታዋቂ ከሆኑት ሩጫዎች መካከል ነው።በመሆኑም ብዙም አስፈላጊ መስሎ አልታየንም።አዲስ ዘመን፡- ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ እዚህ ደረጃ ሲደርስ ብዙ ፈተናዎችን አልፎ ነው፣ አሁንም ፈተናዎች አሉበትና ብትጠቅሳቸው፡፡አቶ ኤርሚያስ፡- ባለፉት ጊዜያት ውድድሩን በየክልሉ ለማስፋት እቅድ ነበረን፤ ይሁንና ሃገሪቷ ውስጥ የነበረው ሁኔታ ብዙ ህዝብ ለመሰብሰብም ሆነ እንዲህ አይነት ዝግጅት ለማድረግ ምቹ አልነበረም።ይህም ብዙ ፍላጎቶቻችንን ነው የገታብን።ሌላው ሁሌም ውድድሩ ሲደርስ አሳሳቢ የሚሆንብን የውድድር ስፍራ ጉዳይ ነው።ቦታውን ቀድሞ አለማወቅ በስራችን ላይ ትልቅ ተጽእኖ እያደረሰብን ሲሆን፤ የመወዳደሪያ ቦታውን ሩጫው ሲደርስ ነው የምናውቀው።በመሆኑም ሩጫው የሃገሪቱ ጭምር በመሆኑ በከተማ አስተዳደሩና በሚመለከታቸው ሁሉ ትኩረት ቢሰጥበትና ቋሚ ቦታ ቢሰጠን መልካም ነው። በመጨረሻም ለተሳታፊዎች ይህ ሩጫ ኢትዮጵያዊነትን የሚያጎላ በመሆኑ በተለመደ ጨዋነቱ ሩጫው ላይ እንዲሳተፍና በኃላፊነት ስሜት የከተማዋን ንጽህና እንዲጠብቅም መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።አዲስ ዘመን፡- አቶ ኤርሚያስ አየለ ለሰጠኸኝ ጊዜ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡አቶ ኤርሚያስ፡- እኔም አመሰግናለሁ፡፡አዲስ ዘመን ጥቅም6/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22603
[ { "passage": "በሩጫው ላይ 44 ሺህ ተወዳዳሪዎች ይሳተፋሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን 400 የሚሆኑት ከሌሎች ሀገራት የመጡ ሲሆን 5 አትሌቶች ደግሞ ኤርትራን በመወከል ይሳተፋሉ።\n\n• በሃሰተኛ ዜናዎች \"የሞቱ\" የኪነጥበብ ሰዎች\n\n• በካማሼ ዞን የመንግሥት ስራ ተቋርጧል\n\n• ኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ ተነሳ \n\nበ10 ሺህ ሜትርና በግማሽ ማራቶን ዝነኛ የሆነው አትሌት ዘረሰናይ ታደሰ ውድድሩ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ተገኝቷል።\n\n\"ኢትዮጵያ በመምጣቴ በጣም ደስ ብሎኛል። የውድድሩ አዘጋጆችንም ስለጋበዙኝም አመሰግናለሁ\" ብሏል።\n\nእኤአ የ2012 ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ የሆነው ዩጋንዳዊው ስቴፈን ኪፕሮቲች ውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ አትሌቶች መካከል አንዱ ነው።\n\nየኬኒያ፣ኡጋንዳ፣ ቦትስዋና ሀገራት የመጡ አትሌቶች በውድድሩ ላይ ይሳተፋሉ።\n\nየውድድሩ መነሻና መድረሻውን ያደረገው ስድስት ኪሎ መሆኑን በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል።\n\nየታላቁ ሩጫ የቦርድ ሰብሳቢ የሆነው አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ ውድድሩ በሰላማዊ መንገድ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ጥሪ አቅርቧል። \n\n ", "passage_id": "54e5830f63b89a984fb12180ec7592ea" }, { "passage": "40ሺህ ያኽል ተሳታፊዎች ይካፈሉበታል ተብሎ የሚጠበቀው 4ኛው ዙር የኢትዮጵያ ቡና ቤተሰብ ሩጫ በመጪው እሁድ ነሐሴ 19 መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ እንደሚካሄድ ተገልጿል። ይህን በማስመልከትም የሩጫው አዘጋጅ ኮሚቴ ዛሬ ከሰዓት በኢንተርኮንቲኔንታል አዲስ ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡በመግለጫው ላይ የሩጫውን አዘጋጅ ኮሚቴ በመወከል አቶ ይስማሸዋ ሥዩም፣ ሰለሞን ታምራትና ክፍሌ አማረን ጨምሮ የውድድሩ አጋር የሆነው ሐበሻ ቢራ በንጉስ ማልት ተወካይ በመሆን በጋራ መግለጫውን ሰጥተዋል፡፡መግለጫውን የከፈቱትና የሩጫው አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ይስማሸዋ ሥዩም በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የክለቦች ወጪን በዘላቂነት ለመቋቋም መሠል የደጋፊውን አቅም ለመጠቀም የሚያግዙ ኹነቶች አይነተኛ ሚና እንዲጫወቱ አውስተው በቀጣይ ከሩጫው በተጨማሪ ሌሎች መርሃግብሮችን ለማዘጋጀት መታቀዱን ተናግረዋል ፤ አያይዘው ክለቡ ለመሰል ሁነቶች ትኩረት በመስጠት በቀጣይም ይህንና ተጓዳኝ ጉዳዮችን በበላይነት የሚቆጣጠርና የሚመራ የሥራ ክፍል ለማቋቋም ስለመታቀዱም ገልጸዋል፡፡በፈርቀዳጅነት ይህንን ውድድር በማዘጋጀት በ2007 በተደረገውና የመጀመሪያው ዙር 8ሺህ ተካፋዮች ከተሳተፉበት ውድድር አንስቶ በየዓመቱ በተሳታፊዎች ቁጥርም ሆነ በውድድሩ ጥራት እምርታን እያሳየ የመጣው ውድድር መሆኑን ገልፀው በዘንድሮው ውድድር የተሳታፊዎች ቁጥር ወደ 40ሺህ ከፍ በማለቱ ውድድሩ ከዚህ ቀደም ይደረግበት ከነበረው የክለቡ ተጫዋቾች መኖሪያና የቡድኑ የወደፊት ስታዲየም መገኛ ቦታ ከነበረው ጀሞ ወደ መስቀል አደባባይ ለመዞር እንደተገደዱ ገልፀዋል። በቀጣይም በጥቂት ዓመታት ውስጥ በዓለምአቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ተብሎ (105ሺህ ተሳታፊዎች በማሳተፍ) በጊነስ ቦክ ኦፍ ወርልድ ሪከርድ ከተመዘገቡት ውድድሮች ልቆ የመገኘት ትልም ስለመወጠኑም አቶ ይስማሸዋ ተናግረዋል፡፡ክለቡ ከ12 እስከ 19 ሚልየን ብር ገቢ አገኝበታለሁ ብሎ እየተንቀሳቀሰበት በሚገኘው በዚህ ውድድር የክለቡ አጋር የሆነው ሀበሻ ቢራ በንጉስ ማልት ስም ውድድሩን ስፖንሰር የሚያደርግ ሲሆን በዕለቱ ለጊዜው ማንነቱ ያልተገለፀ የክብር እንግዳ በስፍራው እንደሚገኙም አቶ ይስማሸዋ አያይዘው ገልጸዋል፡፡በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የክለቡ ደጋፊዎች ማኅበር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን ታምራት በበኩላቸው በውድድሩ ዕለት ስለሚኖሩ ጉዳዮች ማብራሪያ ሰጥተዋል። በንግግራቸውም በዕለቱ ከጠዋቱ 12 ጀምሮ ተሳታፊዎች በመስቀል አደባባይ በመገኘት መታደም የሚችሉ ሲሆን የዘንድሮ የሩጫ መነሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ” ቡናና ሻይ -ገነት ሆቴል-ቄራ-ጎተራ-አጎና ሲኒማ – መሿለኪያ በማድረግ መስቀል አደባባይ ላይ የሚጠናቀቅ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ አቶ ሰለሞን አክለውም በቀኑ ከ150 በላይ አስተባባሪዎች የሚኖሩ ሲሆን በእለቱ ኢትዮጵያ ቡና አርማ ካረፈባቸው ቁሶች ውጪ ማንኛውም አይነት የተለየ ይዘት ያነገቡ ቁሶች ይዞ መገኘት በጥብቅ የተከለከለ ስለመሆኑም አሳስበዋል፡፡ሌላኛው የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ክፍሌ አማረ ለከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ምስጋናን አቅርበው በ4 የተለያዩ ቦታዎች የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በሚቀመጡባቸው የስታዲየም ክፍሎች ስያሜ በተሰየሙ ቦታዎች ላይ የተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶች ስለመኖራቸው ጠቁመዋል፡፡በመቀጠል የ4ኛው ዙሬ የመሮጫ መለያውን ይፋ ያደረጉት አቶ ይስማሸዋ ሥዩም የዘንድሮው መለያ ከሌሎች ዓመታት የሚለየው የአሁኑ የመሮጫ መለያ በጀርባው ላይ ከ12 ቁጥር በተጨማሪ በደጋፊዎች ዘንድ በስፋት ጥቅም ላይ ሲውል የሚታየው “ቡና ደሜ ነው” የተሰኘው መፈክር መታተሙ የተለየ እንደሚያደርገው ገልፀው ፤ ይህም መታሰቢያነቱ ለዘመናት ለዚህ ክለብ ደማቸውን ለሰጡ ደጋፊዎቻቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡በመጨረሻም በስፍራው ከተገኙ የመገናኛ ብዙሃን አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት መርሃግብሩ ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡", "passage_id": "f439bffeb1473f24294de4769af8e9f0" }, { "passage": "ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በዓመቱ ከሚያካሂዳቸውና በጉጉት ከሚጠበቁ ትልልቅ ውድድሮች መካከል አንዱ የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ነው። በተያዘው ወር መጨረሻ የሚካሄደው ውድድሩ ከወዲሁ ተጠባቂ ሲሆን፤ ማህበሩ በድረገጹ ላይ በርቀቱ ስኬታማ የሆኑና በውድድሩም ተጽእኖ ፈጣሪ እንደሚሆኑ የሚጠበቁትን ሀገራት ዘርዝሯል። ከአምስቱ ቀዳሚ ሀገራት መካከልም አንዷ ኢትዮጵያ ሆናለች። በረጅም ርቀት አትሌቲክስ ስኬታማ ከሆኑት የዓለም ሀገራት ተርታ የምትመደበው ኢትዮጵያ በዚህ ዝርዝር ባስመዘገበችው ውጤት ተጠቃሽ ስትሆን፤ የምትቀድማት ብቸኛዋ ሀገር ጎረቤቷ ኬንያ መሆኗም ነው በዘገባው የተጠቆመው። ዘገባው እአአ በ2004ዓ.ም በብራሰልስ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከተሳትፎዎቿ መካከል እጅግ የደመቀችበት መሆኑን አንስቶ፤ በተለይ ስኬታማ የሆኑትን አትሌቶችን ስምም ጠቅሷል።43 ዓመታትን ያስቆጠረው የዓለም ሀገር አቋራጭ ውድድር እአአ በ1973 በቤልጂየም የተጀመረ ውድድር ነው። ውድድሩ እአአ እስከ 2011 ድረስ በየዓመቱ ሳይቆራረጥ ሲካሄድ ቢቆይም ከ2013 ጀምሮ ግን በየሁለት ዓመቱ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር ላይ ባላት ተሳትፎ ለመጀመሪያ ጊዜ ውጤት ያስመዘገበችው እአአ በ1981 ሲሆን፤ ሞሃመድ ከድር ባጠለቀው የብር ሜዳሊያ ነው።  በቀጣዩ ዓመትም አትሌቱ ሰዓቱን በማሻሻል ጭምር አሸናፊ በመሆን ኢትዮጵያን በመድረኩ ከወርቅ ሜዳሊያ ጋር ሊያወዳጃት ችሏል። አትሌት በቀለ ደበሌ እአአ በ1983 አሸናፊ ሲሆን፤ ከሁለት ዓመታት በኋላ ወዳጆ ቡልቲ የነሃስ ሜዳሊያ አጥልቋል። እአአ 1986 አበበ መኮንን የብር ሜዳሊያ ባለቤት ከሆነ በኋላ፤ ፊጣ ባይሳ የነሃስ ሜዳሊያ እስኪያገኝ፤ ለአምስት ዓመታት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሜዳሊያ ሰንጠረዡ አልታዩም ነበር።እአአ 1994 በሃንጋሪዋ ቡዳፔስት በተካሄደው ውድድርም ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ለመጀመሪያ ጊዜ የነሃስ ሜዳሊያ በማጥለቅ ስሙን በታሪክ አስጽፏል። ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታት ጥቂት አትሌቶች የብርና የነሃስ ሜዳሊያዎችን ቢያገኙም የወርቅ ሜዳሊያው በበላይነት የተያዘው በኬንያውያን አትሌቶች ነው። ኬንያዊው ፖል ቴርጋት ለአምስት ዓመታት በተከታታይ በማሸነፍም ታሪካዊ አትሌት ነው።እአአ ከ2012 ጀምሮ ግን የበላይነቱ ከኬንያዊው አትሌት ወደ ኢትዮጵያዊው ወጣት የተሸጋገረበት ነበር። እስካሁንም በመድረኩ አቻ ያልተገኘለት ቀነኒሳ በቀለ ለአምስት ጊዜያት በተከታታይ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ሲሆን፤ ከአንድ ዓመት እረፍት በኋላ በድጋሚ ወርቅ በማጥለቅ በ12 ኪሎ ሜትር ውድድር የስድስት ጊዜ ሻምፒዮን በመሆን ወርቃማ ታሪኩን አስመዝግቧል። ቀነኒሳ በዚህ ውድድር አጭር ርቀትም ስኬታማ ሲሆን፤ አምስት የወርቅና አንድ የብር በአጠቃላይ ስድስት ሜዳሊያዎችን የግሉ በማድረግም ባለ ክብረወሰን ነው።    እአአ በ2004 በብራሰልስ በተካሄደው ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለ፣ ገብረእግዚአብር ገብረማርያም እና ስለሺ ስህን በሰከንዶች ልዩነት ተቀዳድመው ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ የወሰዱበት ውድድር እስካሁንም እጅግ ስኬታማው ነው። አትሌት ገብረእግዚአብሄር ገብረማርያም አንድ የወርቅ ሁለት ብር ሜዳሊያዎችን ሲያስመዘግብ (በአዋቂዎች ዘርፍ)፤ ስለሺ ስህን አንድ የብርና የነሃስ ሜዳሊያ ከመድረኩ አግኝቷል። አትሌት ኢማና መርጋ እአአ በ2011 እና 2013 የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ አሸናፊ ሲሆን፤ ሙክታር እድሪስና አባዲ ሃዲስ ደግሞ የነሃስ ሜዳሊያ ያስመዘገቡ አትሌቶች ናቸው። በሴቶች በኩል ኢትዮጵያ ከሜዳሊያ የተወዳጀችው በኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ ሲሆን፤ ለሶስት ተከታታይ ዓመታትም ድሉ የኢትዮጵያውያን ነበር። እአአ በ1995 እና 1997 በደራርቱ በ1996 ደግሞ በጌጤ ዋሚ የወርቅ ሜዳሊያው ተወስዷል። ሁለቱ አትሌቶች በየዓመቱ እየተፈራረቁ የቆዩ ሲሆን፤ በተለይ አትሌት ጌጤ ዋሚ ሁለት የወርቅ፣ ሁለት የነሃስ እና ሁለት የብር ሜዳሊያዎችን በማግኘት ስኬታማ አትሌት ናት። ወርቅነሽ ኪዳኔ፣ መሪማ ደንቦባ፣ እጅጋየሁ ዲባባ፣ መሰለች መልካሙ እና መስታወት ቱፋም ሜዳሊያ ያስመዘገቡ አትሌቶች ሲሆኑ፤ ጥሩነሽ ዲባባ ደግሞ ሶስት ወርቅ እና አንድ ብር በማግኘት ከስኬታማ አትሌቶች መካከል ትመደባለች። ጥሩነሽ በአጭር ርቀትም አንድ የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ያገኘች አትሌት ናት። አትሌት ህይወት አለሙ፣ ሰንበሬ ተፈሪ፣ በላይነሽ ኦልጂራ እና ነጻነት ጉደታም በቅርብ ዓመታት የሀገራቸውን ስም ማስጠራት የቻሉ አትሌቶች ናቸው።በተመሳሳይ በአዋቂ ወንድና ሴት በቡድን ውጤትም ኢትዮጵያ የተሻለ ታሪክ ያላት ሲሆን፤ በወንዶች 10 የወርቅ፣ 13 የብር እና 7 የነሃስ ሜዳሊያዎችም ተመዝግበዋል። በሴቶች ደግሞ 11 የወርቅ፣ 12 የብር እና 1 የነሃስ ሜዳሊያዎች ተገኝተዋል። ከዚህ ባሻገር በርካታ አትሌቶች በወጣቶች፣ በአጭር ርቀት ሀገር አቋራጭ እንዲሁም በየርቀቱ በቡድን የሜዳሊያ ባለቤቶች ሆነዋል።ማህበሩ ከኢትዮጵያ ባሻገር በዘርፉ ስኬታማ የሆኑትን ሀገራት አንስቷል። ኬንያ ለሶስት አስርት ዓመታት በስኬታማነት የቆየች ሀገር ስትሆን፤ በተለይ ከ2010 ወዲህ በርካታ ሜዳሊያዎችን በማስመዝገብ ላይ ያለች ሀገር መሆኗም ተጠቁሟል። በወንዶች በኩል ኒውዝላንድ እና አሜሪካ ሲጠቀሱ በሴቶች ደግሞ ፖርቹጋል ትጠቀሳለች።አዲስ\nዘመን የካቲት 25/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "b2f5f5f6a9d5972caf959e388b776e5b" }, { "passage": "የዓለማችን ታላላቅ ከተሞች በየዓመቱ ከሚያ ስተናግዷቸው በርካታ የማራቶን ውድድሮች በሚያፎካክራቸው አትሌቶች ደረጃና ጥራት ቀዳሚ ሆኖ የሚገኘው የለንደን ማራቶን ነው። ይህ ውድድር የፊታችን እሁድ ሲካሄድ እንደተለመደው በርቀቱ ስመ ጥር የሆኑ በርካታ አትሌቶችን በሁለቱም ፆታ ለማፎካከር ተዘጋጅቷል። ባለፉት ሦስት ዓመታት በኬንያዊው የርቀቱ ፈርጥና የዓለም ክብረወሰን ባለቤት ኢሉድ ኪፕቾጌ የበላይነት ተይዞ የቆየው የለንደን ማራቶን ዘንድሮ በአገሩና በደጋፊው ፊት በሚሮጠው ሞሐመድ ፋራህ ይደምቃል ተብሎ ይጠበቃል። የዘንድሮው ውድድር በሦስት ጊዜ ባለ ድሉ ኪፕቾጌና በፋራህ መካከል የሚደረገው ፉክክር ከወዲሁ ትኩረት ቢያገኝም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርቀቱ አስደናቂ ብቃት እያሳዩ በሚገኙት ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ሹራ ቂጣታ፣ ሞስነት ገረመውና ልዑል ገብረሥላሴ የበለጠ እንደሚደምቅ ይጠበቃል። በሁለት ኦሊምፒኮችና በሦስት የዓለም ቻምፒዮናዎች የአምስትና አስር ሺ ሜትር ንጉሥ ሆኖ መዝለቅ የቻለው ሞ ፋራህ ካለፈው ዓመት ወዲህ ፊቱን ወደ ማራቶን መመለሱ ይታወቃል። ባለፈው የለንደን ማራቶን ሦስተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ፋራህ ጥቅምት ወር ላይ በቺካጎ ማራቶን በ2:05:11 የአውሮፓን ክብረወሰን አስመዝግቦ የመጀመሪያ ድሉን ካጣጣመ ወዲህ የዓለማችን የወቅቱ ኮከብ የማራቶን አትሌቶችን ጎራ ተቀላቅሏል። ድንቅ የማራቶን አትሌት መሆኑን ለማወጅም የእንግሊዝ መገናኛ ብዙኃን የእሁዱን የለንደን ማራቶን ድል አሰፍስፈው እየጠበቁ ይገኛሉ። ጥያቄው ግን ሌላው ይቅርና ፋራህ ኪፕቾጌን ማቆም እንዴት ይቻለዋል ነው? አንዳንድ የአገሬው መገናኛ ብዙኃን ኪፕቾጌ ምንም ያህል የርቀቱ ኮከብና ባለ ክብረወሰን ቢሆን ከእድሜው መግፋት ጋር ተያይዞ አንድ ቀን እጅ እንደሚሰጥ እርግጠኛ ሆነዋል። ያም ቀን የፊታችን እሁድ ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን እያስቀመጡ ነው። ያም ሆኖ ኪፕቾጌ አሁን ያለው አቋም ካለፈው ዓመት አኳያ የተሻለ እንጂ የባሰ እንደማይሆን ከልምምዶቹ መረዳት ይቻላል። ኪፕቾጌ ባለፈው ዓመት ወደ ተመሳሳይ ውድድር ከመምጣቱ በፊት በተለያዩ ውድድሮች ማራቶንን ከ2፡00 በታች ለማጠናቀቅ ብዙ ጥረት አድርጎ ነበር። ይህም ከአቅሙ በላይ ጉልበቱን እንዲያሟጥጥ አድርጎታል በሚል የለንደን ማራቶንን እንደማያሸንፍ ተጠርጥሮ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ድንቅ ኬንያዊ ለሦስተኛ ጊዜ ለንደን ላይ ነግሷል። ከዚያም ባለፈ ባለፈው የበርሊን ማራቶን 2:01:39 የሆነውን የዓለም ክብረወሰን በአስደናቂ ብቃት የግሉ ማድረግ ችሏል። ኪፕቾጌ በርሊን ላይ ያስመዘገበው ክብረሰወን የብቃቱ ጥግ ነው። ይህን ብቃቱን ዘንድሮ ላይደግመው ቢችል እንኳን ባለፉት ሦስት የለንደን ማራቶኖች ሲያሸንፍ ያስመዘገባቸው ሰዓቶች በአማካኝ ሲሰሉ 2:04:01 ነው። ታዲያ ፋራህም ይሁን ሌሎቹ ጠንካራ ተፎካካሪዎች ይህን እንዴት መመከት ይቻላቸዋል የሚሉ የስፖርቱ ቤተሰቦች በርካታ ናቸው። ኪፕቾጌ የዓለም ክብረወሰን የሆነውን ሰዓት ማስመዝገብ የቻለው በሂደት እየበሰለ መጥቶ በአስራ አንደኛው የማራቶን ውድድሩ ነው። እድሜው ሰላሳ አራት ሲሆን ሞ ፋራህን በሁለት ዓመት ብቻ ይበልጠዋል። ፋራህ እንደ ቀደምቶቹ ኮከብ አትሌቶች ወደ ማራቶን የመጣው በርካታ ዓመታትን በመም ውድድሮች አልፎ መሆኑ በማራቶን ጥሩ አትሌት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ባለፈው ዓመት በመጀመሪያ የማራቶን ውድድሩም ሦስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ የነበረው በራስ መተማመንና በልምድ የሚበልጡትን የስነ ልቦና ጫና መቋቋም መቻሉ ዘንድሮ የተሻለ ነገር እንዲያሳይ ይረዳዋል የሚል መደምደሚያ ላይ አድርሷል። ሁለቱ ታላላቅ አትሌቶች ቀድመው ከገነቡት ስም አኳያ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን በፉክክሩ ግንባር ቀደም ሆነው ይጠቀሱ እንጂ ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ያልተገመተ ነገር ሊፈጥሩ እንደሚችሉ መጠበቅ ያስፈልጋል። በተለይም ባለፈው ዓመት በዚሁ ውድድር ኪፕቾጌን ተከትሎ ሁለተኛ በመሆን ያጠናቀቀው ሹራ ቂጣታ ፋራህን በ1፡ 32 ሰከንድ ልዩነት ቀድሞ መግባቱ ሊሰመርበት ይገባል። በሌላ በኩል ባለፈው የዱባይ ማራቶን የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል ያሸነፋው ሞስነት ገረመው ፋራህ በቺካጎ ማራቶን ሲያሸንፍ በአስራ ሦስት ሰከንዶች ዘግይቶ ሁለተኛ ማጠናቀቁ በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ሌላኛው ትኩረት የሚሰጠው ኢትዮጵያዊ ልዑል ገብረሥላሴ ባለፈው ዓመት ማራቶንን ከ2፡05 በታች ማጠናቀቅ ከቻሉ ሦስት አትሌቶች አንዱ እንደመሆኑ ቀላል ተፎካካሪ አይሆንም። ይህ አትሌት በዱባይ ማራቶን 2፡ 04፡02 ያስመዘገበ ሲሆን ቫሌንሲያ ላይ 2፡04፡ 31 በሆነ ሰዓት የቦታውን ክብረወሰን ማሻሻል ችሏል። ስለዚህ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ከፋራህ ይልቅ ለኪፕቾጌ አስፈሪ ሊሆኑ የሚችሉት ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ናቸው። እንደ ዘንድሮው የለንደን ማራቶን የትኛውም የማራቶን ውድድር በሴቶች ድንቅ የሆነ ፉክክር እንደማይታይ ከወዲሁ እየተነገረ ነው። በሴቶች መካከል ተፎካካሪ የሚሆኑት አትሌቶች ባለፈው ጥር ይፋ ሲደረጉ ከ2018 የወርልድ ማራቶን ሜጀርስ (WMM) ስድስት አሸናፊዎች አምስቱ መካተታቸው ጉድ ተብሎለት ነበር። ከነዚህ በተጨማሪ የ2018 የዱባይ ማራቶን ቻምፒዮንና በታሪክ በርቀቱ ፈጣን ከሆኑት አምስት አትሌቶች አራቱ መካተታቸው የዘንድሮውን የለንደን ማራቶን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ተጠባቂ አድርጎታል። ከዚያን ጊዜ ወዲህ ግን የተቀየሩ ነገሮች መኖራቸው አልቀረም። የረጅም ርቀት ንግስቷ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ሁለተኛ ልጇን እንደ ፀነሰች መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ የዘንድሮው የለንደን ማራቶን የሴቶች ፉክክር ላይ ቀድሞ የነበረው አሰላለፍ እንደሚቀየር ይጠበቃል። ቀደም ሲል የዓለማችን ሁለተኛ፣ ሦስተኛ፣ አራተኛና አምስተኛ ፈጣን ሰዓት ባለቤት የሆኑ አትሌቶች እንደሚፎካከሩበት የተነገረው ውድድር አሁን ሁለተኛ፣ ስድስተኛ፣ ሰባተኛና ዘጠነኛ ፈጣን ሰዓት ያላቸው አትሌቶች የሚፎካከሩበት ሆኗል። የሦስት ጊዜ የለንደን ማራቶንና የአራት ጊዜ የኒውዮርክ ማራቶን አሸናፊዋ ኬንያዊት ማሪ ኪታኒ የዘመኗ ምርጥ አትሌት ነች። ይህም በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ቀዳሚ የትኩረት ማረፊያ አድርጓታል። የኦሊምፒክ 5ሺ ሜትር ቻምፒዮኗ ቪቪያን ቼሪዮት ያለፈው ለንደን ማራቶን አሸናፊና የኒውዮርክ ማራቶንን ሁለተኛ ሆና ያጠናቀቀች አትሌት መሆኗ በሁለተኛነት ትኩረት አሰጥቷታል። 2:18:11 በሆነ ሰዓት የበርሊን ማራቶንን ክብረወሰን የጨበጠችው ግላዲ ቺሮኖ ትልቅ ትኩረት ያገኘች ሌላኛዋ ኬንያዊት ነች። እነዚህ ግዙፍ ስም ያላቸው ኬንያውያን ከእነሱ እኩል አቅም ያላቸውን የዘወትር ተፎካካሪ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚፎካከሩበት ውድድር አጓጊ ባይሆን ይገርማል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማራቶን ጎልቶ የሚጠራ የኢትዮጵያውያን ስም መካከል ሮዛ ደረጄ አንዷ ናት። 2:19:17 በሆነ ሰዓት ባለፈው ዓመት የዱባይ ማራቶን ክብረወሰንን ሰብራለች። ባለፈው የካቲት ደግሞ በባርሴሎና ግማሽ ማራቶን 66፡01 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችላለች። ሮዛ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ለኬንያውያን ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል። ባለፈው ቶኪዮ ማራቶን 2:19:51በሆነ ሰዓት ስታሸንፍ የቦታውን ክብረወሰን በአራት ሰከንዶች ከማሻሻል የቀረችው ብርሃኔ ዲባባ በእሁዱ ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ እንደምትሆን ትጠበቃለች።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 17/2011 ", "passage_id": "f9e47a6c3e9aba6b3a6876efad7b1929" }, { "passage": "ያለፈው የፈረንጆች መስከረም ወር የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ አነጋጋሪና ታሪካዊ ክስተቶችን ያስተናገደ ነበር። በተለይም በማራቶን ውድድር ኬንያዊው አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ በቬና ማራቶን ከሦስት ሳምንት በፊት ለማመን የሚከብደውን አርባ ሁለት ኪሎ ሜትር ከ2፡00 በታች ሮጦ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያሳየበት ውድድር አሁንም ድረስ መነጋገሪያነቱ ቀጥሏል፡፡ በሃያ አራት ሰዓት ልዩነት ውስጥ ሌላኛዋ ኬንያዊት ብሪጊድ ኮስጌ ቺካጎ ማራቶን ላይ ለአስራ ሰባት ዓመታት ሳይሰበር የቆየውን የዓለም ክብረወሰን ማሻሻሏ ታሪካዊና አነጋጋሪ ከመሆን አልፎ የውዝግቦች መነሻ ሆኗል፡፡ የውዝግቡ መነሻ ሁለቱ አትሌቶች የሰሩት ታሪክ ሳይሆን ታሪክ የሰሩበት የመሮጫ ጫማ ነው፡፡ ግዙፉ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ ማራቶንን ከ2፡00 በታች መሮጥ ይቻል ዘንድ ባለፉት ዓመታት ትልቅ ፕሮጀክት ቀርፆ ከኬንያዊው አትሌት ኪፕቾጌ ጋር በጋራ ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ይህም እንዲሳካ ፍጥነትን የሚጨምር ልዩ የመሮጫ ጫማ ከማዘጋጀት ጀምሮ ያልቆፈረው ጉድጓድ አልነበረም፡፡ ይህ ፕሮጀክቱ ተሳክቶም ኪፕቾጌ በአርባ አንድ አሯሯጮችና በዘመናዊው ጫማ ታግዞ አርባ ሁለት ኪሎ ሜትሩን 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማጠናቀቅ ችሏል፡፡ ሌላኛዋ ኬንያዊት ኮስጌም በቺካጎ ማራቶን በቅርብ ዓመታት ይሰበራል ተብሎ ያልተጠበቀውን የፓውላ ራድክሊፍ 2፡15፡25 የሆነ የዓለም ክብረወሰን በዘመናዊው የናይኪ ጫማ ሮጣ በሰማንያ አንድ ሰከንድ አንክታዋለች፡፡ ኪፕቾጌ ይህን ታሪክ ለመስራት ከሦስት ዓመት በፊት ሲነሳም ከተለያዩ የስፖርት ቤተሰቦች ተቃውሞ ማስተናገዱ አልቀረም። ማራቶንን የሰው ልጅ በተፈጥሯዊ መንገድ ከ2፡00 በታች ማጠናቀቅ እየቻለ በቴክኖሎጂ መታገዙ በበርካቶች ዘንድ አልተዋጠም ነበር፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ጀግኖች አትሌቶች ኃይሌ ገብረስላሴና ቀነኒሳ በቀለን ጨምሮ ማራቶንን በቴክኖሎጂ ታግዞ ከ2፡00 በታች መሮጥ እንደማይዋጥላቸው ይልቁንም በተፈጥሯዊ መንገድ ጠንካራ ዝግጅት ተደርጎ ሃሳቡን ማሳካት እንደሚቻል ገና ከውጥኑ ሲናገሩ ነበር፡፡ ኪፕቾጌ ያሳካው ፕሮጀክት በስፖርቱ ትልቅ መነቃቃትን ከመፍጠር ባሻገር የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ግንዛቤ ፈጥሯል፡፡ ይሁን እንጂ ይህን ስኬት በርካቶች ከስፖርታዊ ኩነቱ ነጥለው በመመልከት አትሌቱ ተጫምቶት የሮጠበትን የናይኪ ጫማ የማስተዋወቅ የንግድ ስራ አድርገው ተመልክተውታል፡፡ በንግዱ ዓለም ፍልስፍና ብዙ የሚዋጥ ባይሆንም ናይኪ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ በመላው ዓለም ትልቅ ስም እያለው በዚህ መንገድ ስፖርቱን ተጠቅሞ ምርቱን ለማስተዋወቅ መሞከሩ ሌሎች ተፎካካሪዎቹን ለመዋጥ ያደረገው ስግብግብነት እንደሆነ ያስቀመጡ ወገኖችም ጥቂት አይደሉም፡፡ የሰው ልጅ በተፈጥሯዊ መንገድ ሮጦ ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች ማጠናቀቅ እየቻለ ኪፕቾጌ በምቹ የውድድር ቦታ ላይ በረቀቀ ቴክኖሎጂ ታግዞ ማሳካቱ ከስፖርት መርህ ጋር ተቃራኒ እንደሆነ የሚያነሱም አሉ፡፡ በአርቴፊሽያል ነገሮች በአትሌቲክሱ መግባት ከጀመሩ ወደ ፊት ስፖርቱ አሁን ያለውን የፉክክር ለዛ ይዞ አይቀጥልም የሚል ስጋት ያላቸው የስፖርት ቤተሰቦች ከዚህም ከዚያም አትሌቲክሱ ላይ ጠንከራ ጥያቄና ትችት ሲሰነዝሩ ሰንብተዋል፡፡ ዛሬም ድረስ በበርካታ የቀድሞ የዓለማችን አትሌቶች ተቃውሞ እየገጠመውም ይገኛል፡፡ ዘ ታይምስ እንደ ዘገበው በርካታ አትሌቶች ናይኪ ባሰናዳው ዘመናዊ የመሮጫ ጫማ ላይ የተቃውሞ ድምፅ እያሰሙ ይገኛሉ። የቀድሞው ጣሊያናዊ የማራቶን ቻምፒዮን ጂያኒ ዲማዶናን ጨምሮ ሃያ አትሌቶች ተሰባስበው ለዓለም አትሌቲክስ የናይኪን ዘመናዊ ጫማ ተቃውመው ደብዳቤ አስገብተዋል፡፡ የዓለም አትሌቲክስ ህግ ‹‹የመሮጫ ጫማዎች አትሌቶች እግራቸው ላይ ጉዳት እንዳይደርስባቸውና በምቾት እንዲሮጡ እንጂ ተገቢ ያልሆነ ጥቅምና ድጋፍ እንዲያገኙ አይደለም›› ይላል፡፡ ኪፕቾጌ ማራቶንን ከ2፡00 በታች ሲያጠናቅቅ የተጫማው ጫማ ግን ናይኪ በቴክኖሎጂ የተጠበበትና ገና ለገበያ ያልዋለ እንደመሆኑ ልዩ ትቅም ወይም ድጋፍ አላገኘበትም ማለት አይቻልም፡፡ ኮስጌ በእንግሊዛዊቷ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ለአስራ ስድስት ዓመታት ተይዞ የቆየውን 2፡15፡25 ክብረወሰን በሰማንያ አንድ ሰከንድ ስታሻሽልም ይሄንኑ ጫማ አጥልቃ ነው የሮጠችው፡፡ ይህም መሮጫ ጫማ ፓውላ ራድክሊፍ ክብረወሰን ስትሰብር ከተጫመችው ከ60 እስከ 90 ሰከንድ አትሌቷን የማፍጠን ጥቅም ስላለው ያሻሻለችውን 81 ሰከንድ ላይ ጉልህ ተፅዕኖ እንደነበረው የተለያዩ ትንታኔዎች ወጥተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ዓለም አትሌቲክስ ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂዎች በተለይም ከመሮጫ ጫማው ጋር ተያይዞ ለአትሌቶች እገዛ ማድረግ አለባቸው የለባቸውም የሚለው ሃሳብ አከራካሪ መሆኑን ገልፃል፡፡ ስለዚህም ጫማው በአትሌቶች ፍጥነት ላይ የሚኖረውን ተፅዕኖ ለመመርመር አንድ የጥናት ቡድን ለማቋቋም ተገዷል፡፡ አትሌቶች በተለያዩ ጊዜዎች በሚመረቱ ጫማዎች ሮጠው የተለያዩ ክብረወሰኖችን ሲሰብሩ ቆይተዋል፡፡ ይህ የናይኪ አዲስ ጫማ ከገበያ አኳያ ብዙ ስለተወራለት እንጂ ከዚህ ቀደም የሌለ ነገር እንዳልሆነ የሚሞግቱ የአትሌቲክስ ቤተሰቦች ቁጥርም ቀላል አይደለም፡፡ እንደ ዘ ታይምስ ትንታኔ ከሆነ ናይኪ አዲስ ያመረተው ጫማ ለአንድ አንድ አትሌቶች ይፋ የተደረገው ከ2016 በፊት ነው፡፡ 2014 ላይ ዴኒስ ኪሜቶ በበርሊን ማራቶን 2፡2፡57 የሆነ የዓለም ክብረወሰን ሲያስመዘግብ ይህን ጫማ ተጫምቷል፡፡ ከዚያ በኋም አምስት ጊዜ ይህን ጫማ ያጠለቁ አትሌቶች ክብረወሰን አሻሽለዋል። ይህን ልብ ያሉት የፕሮፌሽናል አትሌቶች የብቃት አሰልጣኝ ስቲቭ ማግኔስ ‹‹ጥናቶችን ካስተዋልን ጫማው በአትሌቶች ፍጥነት ላይ ትልቅ ተፅዕኖ አለው›› በማለት ለዋሺንግተን ፖስት አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አዲስ ዘመን ጥቅምት24/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "cd169a8119d5071dcc10f893ddb937c8" } ]
4b966f7dda5055dc84699757de471b1a
417097662726bcc1924106189587c501
ፕሪሚየር ሊጉ እንዲጀመር ክልሎች የጸጥታ ማረጋገጫ አልሰጡም
ክልሎች ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ማረጋገጫ አለመስጠታቸው የፕሪምየር ሊጉን መካሄድ አሳሳቢ እንዳደረገው አብይ ኮሚቴው ለብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት ገለጸ።ምክር ቤቱም የስፖርቱ ተዋናዮች ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ጠቁሟል። በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይመራ የነበረው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከዚህ ዓመት ጀምሮ አዲስ በተቋቋመው አቢይ ኮሚቴ የበላይነት እንደሚካሄድ መወሰኑ ይታወቃል።የውድድር ዓመቱን ህዳር 13 እና 14 ለማስጀመር ዕቅድ የያዘ ሲሆን፤ ትናንት በተቀመጠው መርሐ ግብር መሰረት በአዳማ ከተማ እጣ የማውጣት ስነስርዓት አካሂዷል።ይሁን እንጂ የክልል ጸጥታ አካላት በደህንነት ዙሪያ አስተማማኝ ማረጋገጫ እንዲሰጡ በደብዳቤ ቢጠየቁም ምላሽ አለመስጠታቸውን የኮሚቴው ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ከትናንት በስቲያ በተካሄደው የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት ማቋቋሚያ ጉባኤ ላይ ገልጸዋል፡፡ኮሚቴው ምላሽ አለመስጠቱን ተከትሎ በድጋሚ ደብዳቤ ወደ ክልል ጸጥታ አካላት ቢልክም ማረጋገጫውን አስካሁን ማግኘት አልተቻለም።አንዳንድ ክልሎች በበኩላቸው በከተማ ደረጃ ብቻ ምላሽ መስጠታቸው ግራ አጋቢና የውድድር ዓመቱን ለማስጀመር አስተማማኝ እንዳልሆነም በሰብሳቢው ተጠቁ ሟል። በመሆኑም ምክር ቤቱ ሁኔታውን አመዛዝኖ ውሳኔ እንዲሰጥበት ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤቱ ሰብሳቢ የሆኑት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በበኩላቸው ሁሉም የስፖርቱ ተዋናዮች ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።ኮሚቴው በደብዳቤ ከመጠየቅም ባለፈ ምናልባትም ኃላፊዎቹ ስራ ሊበዛባቸው ስለሚችል ትኩረት ካልሰጡት በአካል ክልሎች ድረስ በመሄድ መወያየት እንዳለባቸውም ምክረ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል።ከዚህም ባሻገር ምቹ ሁኔታዎችን ተመልክቶ ሊግ ማስጀመሪያውን ጊዜ ማመቻቸት እንደሚገባ በማንሳት መንግስት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚነጋገሩና ጊዜ ወስደው እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። አዲስ ዘመን ጥቅም6/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=22608
[ { "passage": "በኢትዮጵያ በተለይ እግር ኳሱ ስፖርት ለሰላም፣ለጤንነት የሚለው ዜማ ተገልብጦ ለጦርነት ከሆነ ሰንበት ብሏል። እግር ኳሱ ክፉኛ በሆነ መልኩ “ዘረኝነት” በሚባል ጊዜ አመጣሽ በሽታ ሽምድምድ ብሎ ከስታዲየም ውጪ ተኝቷል። የበሽታው ደረጃ በዚሁ ከቀጠለ እስከ ሞት ሊያደርሰው እንደሚችል በስፖርቱ አዋቂዎች በኩል በተደጋጋሚ የሚሰነዘር ምክረ ሃሳብ ሆኗል። በተለይ በ2011 ዓ.ም\nየውድድር ዓመት በእግር ኳስ ሜዳዎች ፈር የለቀቀ ስርዓት አልበኝነት፣ ግጭትና ሁከት በሰፊው ተንጸባርቋል። ከስፖርቱ አውድ ውጪ በሆነ መልኩ እግር ኳሱ ፖለቲካም ጭምር ሆኗል ታዝበናል። የስፖርቱ ባህሪ ባልሆነ መልኩም እነዚህ ተግባራት ስታዲየም ገብተው ተመልክተናል። ችግሩ ዓይን ባወጣ መልኩ የመፈጸሙ ሁኔታ እግር ኳሱን ከመዝናኛ አውዱ አውጥቶ የስጋት አውድማ አድርጎታል። በ2011 በዚህ ሂደት ውስጥ ያለፈው የኢትዮጵያ እግርኳስ የዓመቱ መርሐግብር ፍፃሜውን ቢያገኝም የችግሩ ዳፋ ወደ መጪው የውድድር ዓመት እንዳይሸጋገር ከወዲሁ የቤት ስራዎች በብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በኩል እየተሰሩ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ከ2012 ዓ.ም ስያሜያቸው ብሄር ተኮር የሆኑ የእግር ኳስ ክለቦች ስያሜያቸውን እንዲያስተካክሉ ይደረጋል ሲል ከሰሞኑ ፌዴሬሽኑ ያስተላለፈው ውሳኔ አንዱ ማሳያ ነው። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ እግር ኳሱ በተለየ መልኩ እየማቀቀ ካለው በሽታው እንዲፈወስ የሚያደርገው ጥረት የሚበረታታ ቢሆንም፤ ይህ አይነቱ ውሳኔ የተጠናና የሃገሪቱን ክለቦች ነባራዊ ሃቅን ያገናዘበ ስለመሆኑ ጥያቄን ያስነሳል። የብሄራዊ ፌዴሬሽኑ እንዲህ አይነት ውሳኔ ከማስተላለፍ ጀርባ «በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ቅኝቱን የቀየረው የስፖርታዊ ጨዋነት ችግር የክለቦች ስያሜ ብሄር ተኮር ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ ነው» የሚል አቋም እንዳለው ያመላክታል። በእግር ኳሱ ዘረኝነት ብሄርተኝነት የሚንጸባረቅ መሆኑን የአደባባይ ሚስጥር ቢሆንም፤ በሊጉ ብሄር ተኮር ስያሜ የያዙ ክለቦችን ከሁለትና ሦስት ክለቦች ውጪ አሉ ብሎ ለማስቀመጥ የሚቸግር ነው። ወደ ደቡብ ስንሻገር ወላይታ ዲቻ፣ ሲዳማ ቡና ብሄር ተኮር ስያሜን የያዙ ክለቦች እንደሆኑ መጥቀስ ይቻላል። በፕሪሚየር ሊጉ እየተንጸባረቀ ላለው ችግር በሁለቱ ክለቦች ደጋፊ መካከል ፍጥጫውን በተለያዩ ጊዜያት ታዝበናል። ሆኖም ይህ በችግሩ ላይ እንደ እርሾ ሊታይ የሚችል እንጂ ዋነኛ ተደርጎ ለማቅረብ የሚያዳግት ነው። ፋሲል ከነማ ፣መቐለ ሰባ እንደርታ ፣ባህርዳር ከነማ ፣ሃዋሳ ከነማ ፣ድሬዳዋ ከነማ ፣ስሁል ሽረ ፣ደደቢት ፣ጅማ አባ ጅፋር …ሌሎች ያልተጠቀሱት ክለቦች የፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ መሆናቸው ይታወቃል። ብሄር ተኮር ስያሜን የያዙት ክለቦች የትኞቹ እንደሆኑ ግልጽ ማድረግ የሚገባውና አሻሚ ሃቅ መሆኑን ከስፖርቱ ቤተሰብ በኩል የሚነሱ ሃሳቦች ናቸው። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ከተጠቀሱት ክለቦች ውስጥ የትኞቹ ክለቦች ብሄር ተኮር ስያሜን እንዳልያዙ መናገር ይቻላል። የፌዴሬሽኑ ውሳኔ ቀጣይ ለሚመጡት ክለቦች? ወይስ አሁን ላሉት የሚለው ጉዳይ አሻሚ እንዲሆን ያደርጋል። ችግሩ የታየው ደግሞ ገና በሚመጡት ላይ ሳይሆን አሁን ባሉት እንደመሆኑ በምን አግባብ ይሆን ከሁለቱ ክለቦች ውጪ ያሉትን ክለቦች ብሄር ተኮር ስያሜን የያዙ መያዛቸውን መለየት የሚቻለው። እነዚህ ጉዳዮች ከብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በኩል ማብራሪያን የሚፈልጉ ከመሆናቸው ባሻገር ፌዴሬሽኑ የችግሮቹን መሰረት በአግባቡ ተረድቷል ወደሚል እሳቤ አይወስዱም። ምክንያቱም በፕሪሚየር ሊግ የሚገኙ ክለቦች አብዛኛዎቹ ከተማ አቀፍና ተቋማዊ መሰረት ያደረጉ እንጂ ብሄርን መሰረት ያደረጉ አይደሉም። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ አካሄዱን ዘወር ብሎ መፈተሽ የሚገባው በከተማም ሆነ በተቋም ደረጃ የተደራጁት ክለቦች ደጋፊዎች የሚመነጩት ክልልን ፣ዘርን ፣ብሄርን ፣ማንነትን በለየ ሁኔታ መሆኑን ነው። ደጋፊዎች በክልላቸው እንዳለው ክለብ ብዛት አንድም ፣ሁለትም ፣ሦስትም ቡድንን በእኔነት ስሜት የመደገፍ ዝንባሌን አዳብረዋል። በደጋፊዎች በኩል መፋጠጦቹም ሆነ መቀራረቦቹ በክልል የተቧደኑ ነበሩ። የአንዱ ክለብ ደጋፊ ከሌላው ደጋፊ ሲጋጭና ሲቋሰል የነበረው ወቅታዊ የሃገሪቱን ፖለቲካ በተከተለ መልኩ እንደነበር ለመታዘብ ችለናል። ክለቦች ከቆሙበት ክልል አኳያ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችና የሚፈጠሩ መፋጠጦች፤ በተቃራኒው ደግሞ የወንድማዊነት፣ የወገንተኝነት አዝማሚያዎች በዚህ መልክ የተቃኙ እንደነበረ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነበር። ለዚህም እንደማሳያ መጥቀስ ካስፈለገ ከሻምፒዮናው መቐለ ሰባ እንደርታ ፣ከስሁል ሽረ ፣ከደደቢት ብሎም ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ክለቦች እርስ በእርስ ሲገናኙ የሚስተዋለው የስታዲየም ድባብ የአንድነት ፣የወንድማማችነት አዝሎ ነው። በፋሲል ከነማ ፣ባህርዳር ከነማ ፣ወልዲያ ከነማ ደጋፊዎች መካከል ያለውን ስሜት በተመሳሳይ ስንቃኘው አብሮነት ፣ወንድማዊነቱ ጎልቶና ከፍ ብሎ ይስተዋላል። የስታዲየሙ ድባብም ሆነ የመዝሙሩ ሁናቴ ይቀየራል። ስፖርታዊ ጨዋነቱ ከፍ ብሎ ይስተዋላል። በዚህ መልክ በነበሩ ጨዋታዎች ላይ የስፖርታዊ ጨዋነት ችግሮቸ ከሞላ ጎደል እንጂ ብዙም የጎላ አልነበሩም። የእግር ኳሱን ድባብ የሚቀይረውና ጸብና ስርዓት አልበኝነቱ የሚጎላው የአንዱ ክልል ክብ ከሌላ ክልል ክለብ ጋር በሚደረጉ ጨዋታዎች ላይ ነው። በ2011 ዓ.ም የውድድር ዓመትን ዘወር ብለን በትግራይ ክልል እና በአማራ ክልል ክለቦች መካከል የነበረውን ሁኔታ ስንፈትሽ እውነታውን ያስረዳናል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የስፖርታዊ ጨዋነት ምንጩ የክለቦች ብሄር ተኮር ስያሜ ከመያዛቸው መሆኑን ጠቅሶ «ብሄር ተኮር የሆኑ የእግር ኳስ ክለቦች ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ ስያሜያቸውን እንዲያስተካክሉ ይደረጋል »የሚለው ውሳኔ ዳግም ሊፈተሽ እንደሚገባ ያመላታል። ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ካንሰር የሆነው ብሄር ተኮር ስያሜ ሳይሆን ብሄር ተኮር እሳቤ መሆኑን ሊሰመርበት ይገባል።ብሄር ተኮር ስያሜን የያዙ ክለቦች ያውም በሌሉበት ስያሜው ተቀይሮ አመለካከት ሳይቀየር ለውጥ ወዴት ይገኝ ይሆን ? ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ\nመሬት ያለውን እውነት\nተቀብሎ አመለካከት ላይ መስራቱ\nአንዱና ዋነኛው መፍትሄ\nሊሆን ይገባል። ሌላው\nበዘረኝነት በሽታ በሲቃ\nውስጥ የሚገኘውን እግር\nኳስ መድህን ለማግኘት\nበተለያዩ መድረኮች ሲነሱ\nየነበሩ የመፍትሄ ሃሳቦችን\nዘወር ብሎ መመልከቱም\nመዘንጋት የለበትም። የኢትዮጵያ\nስፖርት እንቅስቃሴ ውስጥ\nየዘር ልዩነት እንዲጠፋ\nየኦሊምፒክና የዓለም አቀፍ\nየስፖርት ማኅበራት ደንብና\nመመሪያዎች እንዲከበሩ ማድረግ\nአንዱና ዋነኛው መፍትሄ\nነው። የብሄራዊ ፌዴሬሽኑ\nየዲሲፕሊን ህግ ዳግም\nመቃኘት ሌላው መፍትሄ\nይሆናል። በእግር ኳሱ የሚስተዋለው የስፖርታዊ ጨዋነቱ\nችግር ቀደም ሲል ከነበረው\nፍጹም የተለየ ነው።\nበመሆኑም ኢትዮጵያ እግር\nኳስ ወቅታዊና ነባራዊ\nእውነት መሰረት አድርጎ\nማዘጋጀት ያስፈልጋል። የሕግ\nየበላይነት እንዲከበር የመንግሥት\nቁርጠኝነትና ውሳኔ እንዲኖር\nማድረግ ተያይዞ የሚነሳ\nመፍትሄ ነው፡፡ አዲስ ዘመን ሀምሌ 8/2011 ", "passage_id": "9be317def1613749b73235a75ec174e7" }, { "passage": "የ 2011 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው መቀሌ 70 ዕንደርታ እና ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው እና የጥሎ ማለፍ ውድድር አሸናፊው ፋሲል ከነማ በአፍሪካ የውድድር መድረክ ተሳታፊ እንዲሆኑ በሊጉ ካምፓኒ ጠቅላላ ጉባዔ ተወሰነ፡፡\nበጠቅላላ ጉባዔው በአፍሪካ መድረክ ኢትዮጵያን የሚወክሉ ክለቦች በ2011 ውጤት ይሁን ወይስ ባልተጠናቀቀው የ2012 ውጤት በሚለው ላይ ውይይት ተደርጎ ነበር፡፡ በውይይቱም በአፍሪካ መድረክ ኢትዮጵያን የሚወክሉ ክለቦች በ2011 ውጤት መሰረት ይሁን የሚለው በድምጽ ብልጫ አሸንፏል፡፡በዚህም መሰረት መቀሌ 70 ዕንድርታ በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ፋሲል ከነማ ደግሞ በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን እንዲሳተፉ ነው ውሳኔ የተላለፈው፡፡\nየመወያያ ርዕስ ሆኖ የቆየው የተጨዋቾች የ50 ሺ ብር የደመወዝ ገደብ በ2013 ዓ.ም ባለበት እንዲቀጥል እና ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም እንደ አቅሙ እንዲከፍልም ተወስኗል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በስያሜያቸው ጥያቄ የተነሳባቸው ክለቦች በራሳቸው ፍቃድ ስያሜያቸውን እንዲቀይሩ መወሰኑንም ተሰምቷል፡፡\nእየተደረገ ባለው ስብሰባ የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ ካምፓኒ በ2013 ዓ.ም ከሊጉ ስያሜ ስምንት ሚሊየን ብር እንደሚጠብቅ አስታውቋል፡፡ ካምፓኒው ከክለቦች ክፍያ ከቴሌቪዥን መብትና ከሊጉ ስያሜ ጋር በአጠቃላይ 29 ሚሊየን ብር ለማግኘት እንዳቀደ አመራሮቹ ገልጸዋል፡፡\nበተያያዘ ዜና የፌዴራል ስፖርት ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጅሎ በስፖርታዊ እንቅስቃሴ ጅማሮ ዙሪያ መግለጫ የሰጡ ሲሆን ውድድሮች ለጊዜው በዝግ እንዲካሄዱ ፤ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ደግሞ ወረርሽኙ ከቀነሰ የተወሰነ ተመልካች እንዲገባ እንደሚደረግና የሌሎች ሀገሮች ተሞክሮ ይህንን እንደሚያመለክት ገልጸዋል፡፡\nዓለም አቀፍ ውድድር ላይ የሚካፈሉ ስፖርተኞችን ጨምሮ ሆቴል ሳይገቡ መጀመሪያውኑ ምርመራ እንደሚያደርጉ የጤናና የጸጥታ ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ በሀገር አቀፍና በክልሎች ስራው እንደሚመራም ምክትል ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡\nይህንን መመዘኛ የማያሟላ እንደሚሰረዝና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም እንደሚከታተለው አስታውቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ከተመሠረቱ ጥቂት ቆይተው የሚፈርሱ ክለቦች እንዳሉ ያነሱት አቶ ዱቤ እነሱን የማጥራትና ደረጃ የመስጠት ሂደት እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡\nየአዲስ አበባ ስታዲየምን በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚታደስ ተናግረዋል፡፡\nየተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው ስብሰባ ጤና ሚኒስቴር ያወጣውን መመሪያዎች በአግባቡ በመተግበር የቱሪዝም እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እንዲካሄዱ በአብላጫ ድምፅ ወስኗል።\n", "passage_id": "56e25ab81e404fb65fb54f3ec529c1a6" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬም ሲቀጥሉ ሲዳማ ቡና ኤሌክትሪክ ላይ ጣፋጭ ድል ተጎናፅፏል፡፡ በኢትዮጵያ ቡና እና ሀዋሳ ከተማ መካከል የተደረገው ጨዋታ ደግሞ በደጋፊዎች ስርአት አልበኝነት ምክንያት ሁለተኛው አጋማሽ ሳይካሄድ ተቋርጧል፡፡በ09፡00 ሲዳማ ቡናን ያስተናገደው ኤሌክትሪክ 5-0 በሆነ ሰፊ ውጤት ተረምርሟል፡፡ ላለመውረድ በሚደረገው ትግል ውዝጥ የሚገኘው ኤሌክትሪክ የቅርብ ተፎካካሪዎቹ ዳሽን ቢራ እና አርባምንጭ ከተማ ትላንት ነጥ በመጣላቸው መልካም አጋጣሚን ማግኘት ቢችልም ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡ ይልቁንም በሲዳማ ቡና ሙሉ የጨዋታ የበላይነት ተወስዶበት ተሸንፏል፡፡የሲዳማ ቡናን የመክፈቻ ግብ በረከት አዲሱ ከማዕዘን ምት የተሸገረውን ኳስ በመጠቀም ሲያስቆጠር የመጀመርያው አጋማሽም በ1-0 ውጤት ተጠናቋል፡፡ ከእረፍት መልስ ይበልጥ ተጠናክረው የቀረቡት ሲዳማ ቡናዎች በፍፁም ተፈሪ ሁለተኛውን በዘነበ ከበደ ግሩም ቅጣት ምት ሶስተኛውን ሲያስቆጥሩ ፈጣኑ የመስመር አማካይ አዲስ ግደይ የመጨረሻዎቹን ሁለት ግቦች አክሏል፡፡11፡30 ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀዋሳ ከተማ ያደረጉት ጨዋታ በእረፍት ሰአት በተፈጠረ የደጋፊዎች ረብሻ ምክንያት ጨዋታው እንዲቋረጥ ተወስኗል፡፡ በጥሩ ድባብ እና ፈጣን እንቅስቃሴ የተጀመረው ጨዋታ በሜዳ ላይ ጉሽሚያዎች ታጅቦ ቀጥሎ ከ30ኛው ደቂቃ በኋላ መልኩን ቀይሯል፡፡ ደስታ ዮሃንስ ያሻማውን ቅጣት ምት ጋዲሳ መብራቴ አግኝቶ ወደ ግብ ሲመታ አቅጣጫው ቀይሮ አስቻለው ግርማ ጋር ሲደርስ የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች ወደ ግብነት ቀይሯታል፡፡ ለግቧ መቆጠር ምክንያት የነበረው ጋዲሳ መብራቴ ከጨዋታ ውጪ በሆነ አቋቋም ላይ እንደነበር በመግለፅ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በእለቱ ዳኛ ላይ ተቃውሞዋቸውን ያሰሙ ሲሆን የፕላስቲክ ጠርሙሶች ወደ ሜዳ መወርወር ጀምረዋል፡፡ አንድ ደጋፊም አጥር ዘሎ በመግባት የእለቱን አርቢቴር ለመደብደብ ሲጋበዝ ተስተውሏል፡፡ከግቡ መቆጠር በኋላ የተቋረጠው ጨዋታ ከ7 ደቂቃዎች በኋላ በድጋሚ እንዲጀመር ተደርጎ የመጀመርያው አጋማሽ ቢጠናቀቅም በሚስማር ተራ የሚገኙ ደጋፊዎች የተሰቀሉ ባነሮችን በመቀዳደድ የጀመሩት ረብሻ በሁሉም የስታድየሙ ክፍል ተዳርሶ ከፍተኛ ትርምስ ተፈጥሯል፡፡ በፌዴራል ፖሊሶች እና በደጋፊዎች መካከል ግጭቶች የነበሩ ሲሆን በስታድየሙ የተመደበው የፀጥታ ሃይል ከነበረው የደጋፊ ብዛት ጋር ተመጣጣኝ ያልነበረ መሆኑ ችግሩን ሲያባብሰው ተስተውሏል፡፡ ሁከቱ በፈጠረው ትርምስ ምክንያትም በርካታ ደጋፊዎች እና የፀጥታ አካላት ተጎድተዋል፡፡ በወንበሮች እና በተሰቀሉ ባነሮች ላይም ጉዳት ደርሷል፡፡ለ1 ሰአት ያህል ከቀጠለው ትርምስ በኋላ ደጋፊዎች ከስታድየሙ እንዲለቁ ተደርጎ በባዶ ስታድየም ጨዋታው እንዲቀጥል ተጫዋቾች ከመልበሻ ክፍል ቢወጡም የአለቱ ኮሚሽነር ጨዋታው እንዲቋረጥ አዘው የሁለተኛው አጋማሽ ሳይካሄድ ቀርቷል፡፡ ሁለተኛው አጋማሽ መቼ እንዲቀጥልም ከውሳኔ ላይ አልደረሰም፡፡የኢትዮጵያ እግርኳስ በዚህ አመት ቁጥሩ የበዛ የደጋፊዎች ግጭት እና ረብሻ ማስተናገዱን ቀጥሏል፡፡ ችግሩም መፍትሄ ሳይገኝለት ከእለት ወደ እለት ስር እየሰደደ መጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሽን እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ቀላል ቅጣቶችን ከማስተላለፍ እና ጣት ከመቀሳሰር ባለፈ የማያዳግሙ የመፍትሄ እርምጃዎች ካልተሰዱ በቀር እየተባባሰ የመጣው የደጋፊዎች ረብሻ ከእግርኳስ ሜዳዎች አልፎ ትልቅ ሃገራዊ ስጋት ወደመሆን መሸጋገሩ አይቀሬ ነው፡፡", "passage_id": "b229a1c206cbb7386932f744aab31585" }, { "passage": " የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ስያሜውን ይዞ መካሄድ ከጀመረ ከሁለት አሥርታት በላይ አስቆጥሯል። ፕሪሚየር ሊጉ እነዚህን ዓመታት ባደረጋቸው ረጅም ጉዞዎች ስያሜውንና ዕድሜውን የሚመጥን ዕድገት እንደሌለው በርካቶች ያነሳሉ። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስያሜ ለውጡን ‹ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ዕድገት በሚል ብቻ ጥናት ሳይደረግ ውድድር መጀመሩ ለዕድገቱ መቀጨጭ የራሱን ድርሻ አበርክቷል ›ሲሉ የሚተቹ በርካቶች ናቸው። ለዚህ በትልቁ የሚጠቀሰው ፕሪሚየር ሊጉን ጨምሮ 98 በመቶ የአገሪቱ ክለቦች በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ከመንግሥት ቋት በመሆኑ እግር ኳሱ ገበያ ተኮር እንዳይሆን አድርጎታል። ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ማንሰራራት የጀርባ አጥንት የሆነውን ፕሪሚየር ሊግ ጠንካራ ማንነት ማላበስ የሚያስችለን አሰራርና አደረጃጀት ማበጀት ያስፈልጋል የሚሉ ድምጾች ሲሰሙ ኖረዋል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የእግር ኳስ ችግር መፍቻ መፍትሄ አንዱ የሊግ አደረጃጀትን ማሻሻል መሆኑን በማመን በ2011 ዓ.ም አጋማሽ ላይ አደረጃጀቱን ለመቀየር ለውይይት ክፍት ባደረገ መልኩ እንቅስቃሴውን አጠናክሯል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዓምና በተቋቋመው «የሊግ ካምፓኒ» እየተመራ ነበር አዱሱን የለውጡን ጅማሮ «ሀ» ያለው። በብሔራዊ ፌዴሬሽንና ክለቦች የጋራ ጥረት ራሱን ችሎ ፕሪሚየር ሊጉን እየመራ ያለው የሊግ ካምፓኒው ከሰሞኑ ያስተላለፈው ውሳኔ በእጅጉ እያነጋገረ ይገኛል። የሊግ ካምፓኒው በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ሐሙስ ሐምሌ 16 ቀን 2012 ዓ.ም. ውይይት አድርጎ ነበር። የኢትዮያ ፕሪሚየር ሊግ ሊግ ካምፓኒ አመራሮቹ ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል «የሊጉን የጥራት ደረጃ ከመጠበቅ ጀምሮ ክለቦቹን ለተለያዩ ችግሮችና አለመግባባቶች ሲዳርጉ ቆይተዋል» በሚል ማሻሻያና ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸው የውድድር ደንብና መመሪያዎች ላይ ውይይት ተደርጓል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሊግ ኩባንያው አዲስ የውድድር ደንብና መመሪያን አጽድቋል። የፕሪሚየር ሊጉ አዲሱ የውድድር መመሪያ በ2021 የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ እና የኮንፌደሬሽን ካፕ ላይ ኢትዮጵያ ተወካይ አልባ አድርጓታል መባሉን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል።የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር መመሪያ በሀገራችን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቢታወጅ እና ያልታሰበ ድንገተኛ ችግር ተፈጥሮ ውድድር ቢቋረጥ በምን መልኩ ውጤት ይሰጥ የሚል የተቀመጠ መመሪያ (ደንብ) አልተዘጋጀም። ስለዚህ አሸናፊ፣ ወራጅ እና በአፍሪካ መድረክ ሀገሪቱን የሚወክል ክለብ በምን መልኩ ይሳተፍ የሚል ህግ እንዳልተቀመጠ ዘገባው አትቷል። የሊግ ካምፓኒ አመራሮች ባደረጉት ውይይት በቀጣይ የውድድር ዘመን በሀገራችን አሁን የተፈጠረው የኮሮና ቫይረስ አልያም ሌላ ከአቅም በላይ ችግር ቢከሰት በምን መልኩ እደሚስተናገድ የሚያስችል አዲስ መመሪያ አውጥተዋል ያለው ዘገባው፤ በመጀመሪያ ደረጃ ውድድሩ ከ75 % ያህል ጨዋታው ተከናውኖ ከሆነ እና ውድድሩ ቢቋረጥ ባለው ውጤት መሠረት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የያዘው ክለብ በካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ እንዲሳተፍ ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው ክለብ ደግሞ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እንዲካፈል ይደረጋል። በወራጅ ላይ የሚገኙ ሶስት ክለቦች በውጤታቸው መሠረት እንዲወርዱ እና በምትካቸው ከከፍተኛ ሊግ አዳጊ ክለቦች እንዲኖሩ በአዲሱ መመሪያ መካተቱን አትቷል።የሊግ ካምፓኒው ውድድሩ ምናልባት ከ65 እስከ 70% ደረጃ ላይ ደርሶ በተለያዩ ምክንያቶች\nቢቋረጥና ውድድሩ በዛው ዓመት ለመቀጠል\nአስቸጋሪ ሁኔታዎች ከሌሉ ምን መደረግ አለበት ለሚለው ውሳኔ አስተላልፏል።\nበውድድር ዓመቱ በፕሪሚየር\nሊጉ አንደኛና ሁለተኛ ሆነው ያጠናቀቁ\nቡድኖች ኢትዮጵያን በአፍሪካ\nመድረክ መወከል እንደሚችሉ\nወስኗል። በዚህ መሰረት የሊግ ኩባንያው\nሊጉን ለመምራት አዲስ ባፀደቀው መመሪያ መሰረት በኢትዮጵያ\nፕሪሚየር ሊግ የ2012\nውድድር ዘመን አሸናፊ ወራጅ እና አዳጊ ክለብ የማይኖር መሆኑን መወሰኑን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል።በ2012 የውድድር ዘመን 56% ላይ የተቋረጠ በመሆኑ፤ አስቀድሞ አጋዥ የሆነ በመመሪያ የተደገፈ ደንብ ባለመኖሩ የሊግ ኩባንያው አስቀድሞ ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዓመት የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ እና የኮንፌደሬሽን ካፕ ላይ እንደማትሳተፍ ባስተላለፈው ውሳኔ እንዲፀና ተደርጓል ብሏል። የሊግ ኮሚቴው ውሳኔ ተከትሎ የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብና መቐለ ሰብዓ እንደርታ በአህጉራዊ መድረክ ላይ ሊሳተፍ ይችሉ ይሆና የሚሉ የተስፋ አስተያየቶች ፉርሽ ያደረገ ተብሏል።የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2012 ውድድር ዓመት\nበኮቪድ 19 ምክንያት\nመቋረጡን ተከትሎ፣ በ‹‹አሸናፊ፣ ወራጅና ወጪ በ2013\nውድድር ዓመት በአፍሪካ\nመድረክ የሚሳተፍ ቡድን የለም፤›› በማለት ሊግ ካምፓኒው\nያሳለፈውን ውሳኔ፣ በተለይ የፕሪሚየር ሊጉ ውድድር እስከሚቋረጥ\nአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ላይ የነበሩት\nፋሲል ከተማና መቐለ ሰብዓ እንደርታ\nበአኅጉራዊ መድረክ የመሳተፍ\nዕድል ሊኖረን ይገባል በሚል ውሳኔውን\nመቃወማቸው አይዘነጋም። የፋሲል ከተማ እግር ኳስ ክለብ ለሊግ ካምፓኒው\nውሳኔው ትክክለኛና ተገቢ እንዳልሆነ ጉዳዩን በደብዳቤ ሲገልጽ ቢቆይም፣ ምንም ዓይነት ምላሽ ሳያገኝ ቆይቶም ነበር።አዲስ ዘመን ሐምሌ 21/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "fcc23edbdff1e39146c76ebdf911645a" }, { "passage": "በ15ኛው ሳምንት መከላከያ ከ ኢትዮጵያ ቡና ባደረጉት ጨዋታ ባሳየው ያለልተገባ ባህርይ በቀይ ካርድ ተወግዶ የነበረው ባዬ ገዛኸኝ በፌዴሬሽኑ ዲሲፕሊን ኮሚቴ የ6 ወራት እገዳ ተላልፎበታል፡፡\nመከላከያ የተወሰነውን ውሳኔ በመቃወም ይግባኝ ጠይቆ የነበረ ሲሆን ይግባኙ እስኪታይ ድረስም አጥቂው የቀይ ካርድ ቅጣቱን ጨርሶ እንዲጫወት ተፈቅዶለት ከሲዳማ ቡና ጋር በተደረገው ጨዋታ ተሰልፎ ግብ ማስቆጠር ችሎ ነበር፡፡\nአሁን ደግሞ የዲሲፕሊን ኮሚቴው በውሳኔው በመፅናት ባዬ ገዛኸኝን ለስድስት ወር እንዳይጫወት አግዶታል፡፡በእስር ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ፕሬዝዳንት እና የደጋፊ ማህበር አመራሮች ክስ ተመስርቶባቸው ዛሬ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ መደበኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት ቀርበዋል፡፡\nበችሎቱ አቃቤ ህግ ምርመራውን ለማጠናከር ይረዳው ዘንድ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው በጠየቀው መሰረት ተጨማሪ ሰባት ቀን (ለሰኔ 13) ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ደደቢት በውጤት ማጣት ከአሰልጣኝ ጌታቸው ዳዊት ጋር ከተለያየ በኋላ በጊዜያዊነት ቡድኑን በተረከቡት ኤልያስ ኢብራሂም እየተመራ ከዳሽን ቢራ ጋር ያደረገውን ጨዋታ በድል ተወጥቷል፡፡\nየክለቡ የቴክኒክ ዳይሬክተር አቶ ሚካኤል አምደመስቀልም ክለቡ በትክክለኛው መንገድ መጓዝ እንደጀመረ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡\n” አሁን ሙሉ ለሙሉ በመጀመርያው ዙር የነበረን ጥንካሬ መመለስ ላይ ነው ። ያሳለፍነው ደካማ ጊዜ ጥሩ ትምህርት ሰጥቶን አልፏል፡፡ ከዳሽን ጋር በነበረው ጨዋታ ላይ ጥሩ እንቅስቃሴ አሳይተናል፡፡ በቀሪው የሊጉ ጨዋታ ላይ ጥሩ ደረጃ ላይ ሆነን መጨረስ እንፈልጋለን ፣ ለቀጣይ አመት ተጠናክረን ለመቅረብ በሚያስፈልጉን ነገሮች ላይም እንሰራለን ” ብለዋል፡፡ የአዳማ ከተማው አማካይ ወንድሜነህ ዘሪሁን በክለቡ መታገዱ ታውቋል፡፡\nክለቡ አማካዩን ለማገድ ከውሳኔ ላይ የደረሰው በዲሲፕሊን ጉዳይ ሲሆን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት እንደነበር ከክለቡ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ የስታድየም ረብሻዎች በመላ ሃገሪቱ እየተዛመቱ ይገኛል፡፡ ትላንት በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አክሱም ከተማ ከ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያደረጉት ጨዋታ መጨረሻም አላማረም፡፡እንግዳው ወልዋሎ በጨዋታው መገባደጃ ደቂቃዎች ባስቆጠረው ግብ ጨዋታው በወልዋሎ 1-0 አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኀላ በሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች መካከል ግጭት ተከስቷል፡፡ የዳኛ ውሳኔ እና በደጋፊዎች መካከል የነበረውን መበሻሸቅ ተከትሎ በተጀመረው ግጭት በርካታ ደጋፊዎች እና የፀጥታ ሀይሎች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ከስፍራው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ግጭቱ እስከ ምሽት በመዝለቁም ተጫዋቾች ሜዳውን ለመልቀቅ እስከ ምሽት 3:30 ድረስ ለመጠበቅ ተገደዋል፡፡በኢትዮጵያ እግርኳስ አልፎ አልፎ ሲከሰት የነበረው የደጋፊዎች ረብሻ አሁን አሁን እየተደጋገመ እና የአስከፊነቱ መጠን በእጅጉ እየጨመረ መጥቷል፡፡ \nልደታ ክ/ከተማ 1-3 ዳሽን ቢራ\nኢትዮጵያ ቡና 1-3 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ\nኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1-0 አፍሮ ፅዮን ባሳለፍነው አርብ በኢትዮዽያ ቡና እና በሀዋሳ ከተማ መካከል በተካሄደው ጨዋታ ላይ በተፈጠረውን የሰው ጉዳትና የንብረት ውድመት አስከትሎ ሊወሰድ ስለሚገባው ውሳኔ ከስፖርት ኮሚሽን ፣ ከሊግ ኮሚቴ ፣ ከዲሲፒሊን ኮሚቴ አና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ረጅም ሰአት የፈጀ ስብሰባ እያደረገ ይገኛል፡፡ነገ የዲሲፒሊን ኮሚቴ በሚያደርገው ስብሰባ ደግሞ በሁለት መሰረታዊ ነገሮች ላይ እንደሚወያይ ይጠበቃል፡፡ የመጀመርያው ጉዳይ ጨዋታው ይቀጥል አይቀጥል የሚለው ሲሆን ለደረሰው የአካል ጉዳት የንብረት ውድመት መተዳደርያ ደንቡን መሰረት ያደረገ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት ነገ በወላይታ ድቻ እና መከላከያ መካከል በሚደረግ ጨዋታ ይጀምራል፡፡ የአርቡን የስታድየም ረብሻ ተከትሎ የአአ ፖሊስ ኮሚሽን የክለቡ ፕሬዝዳንት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞን ጨምሮ የቡድን መሪውን እና የደጋፊ ማህበሩ አመራሮችን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ይታወቃል፡፡\nኮሚሽኑ ለረብሻው ተጠያቂ ናቸው በሚል ክስ የመሰረተባቸው ሲሆን ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡\nበተያያዘ ዜና የአአ ፖሊስ ኮሚሽን የስታድየሙ ሰራተኞች በተፈጠረው ጉዳይ ላይ ቃላቸውን እንዲሰጡ ማድረጉ ታውቋል፡፡ በአፍሪካ ከ20 አመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የመልስ ጨዋታ ጋና ከ ኢትዮጵያ 12:00 ላይ ሊያደርጉት የነበረው ጨዋታ በኬፕ ኮስት ከተማ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ሳይካሄድ ቀርቷል፡፡ ኢትዮጵያም ጨዋታው መካሄድ እንደሌለባት በመግለጿ ጨዋታው ለነ ተዘዋውሯል፡፡በዚህም ምክንያት ጨዋታው ነገ በተመሳሳይ ሰአት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ በከተማው የጣለው ዝናብ ነገም የሚቀጥል ከሆነም ወየ ሌላ ከተማ ሊዞር ይችላል ተብሏል፡፡በሌላ በኩል ብሄራዊ ቡድኑ ዛሬ ጨዋታውን አድርጎ ነገ ወደ አዲስ አበባ ይገባል ተብሎ ቢጠበቅም በ1 ቀን የሚራዘም በመሆኑ ሀሙስ የሚደረጉ የከፍተኛ ሊግ ጨዋታዎች ላይ ሽግሽግ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከ20 አመት በታች ቡድኑ አመሻሽ 12:00 ላይ ጋናን ይገጥማል፡፡ የቡድኑ የመጀመርያ 11 ተሰላፊዎችም የሚከተሉት ናቸው፡፡1 ተክለማርያም ሻንቆ8 እንየው ካሳሁን – 2 ሃይደር ሙስጠፋ – 6 ተስፋዬ ሽብሩ – 7 ደስታ ደሙ16 ዘላለም ኢሳያስ – 13 ዘሪሁን ብርሃኑ (አምበል)17 ዳዊት ማሞ – 11 ዳዊት ተፈራ – 15 ሚካኤል ለማ9 አሜ መሃመድዛሬ መልካ ቆሌ ላይ በወልድያ እና አማራ ውሃ ስራ መካከል ሲካሄድ የነበረው ጨዋታ ሁለተኛው አጋማሽ ሳይደረግ ቀርቷል፡፡ጨዋታው እንዲቋረጥ መንስኤ የሆነው አማራ ውሃ ስራ ጨዋታውን ቢጨርሱ ችግር ሊፈጠር እንደሚችል ስጋታቸውን በመግለፃቸው መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡አማራ ውሃ ስራዎች ጨዋታውን ለመጫወት አስተማማኝ እና ለደህንነታችን በቂ ዋስትና ካልተሰጠን ለመቀጠል እንቸገራለን በማለት ጨዋታውን መቀጠል እንደማይችሉ አሳውቀው መውጣታቸውን የገለፁ ሲሆን ወልድያዎች ደግሞ በተረጋጋ ነገር ውስጥ እረፍት ላይ አንጫወትም በማለታቸው ተቋርጧል ይላሉ፡፡በጉዳዩ ዙርያ የከፍተኛ ሊጉ ሀላፊ አቶ ጌታቸውን ማብራርያ ብንጠይቅም  የኮምሽነሩና የዳኞች ሪፖርት እስካልደረሳቸው ድረስ ይህ ነው ማለት እንደማይችሉ ጠቅሰዋል፡፡የዳሽን ቢራ ዋና አሰልጣኝ ታረቀኝ አሰፋ እና ረዳታቸው ከደደቢት ሽንፈት በኋላ የገቡበት አልታወቀም፡፡ በዛሬው እለትም ዳሽን ቢራ በቡድን መሪውና በአስራት መገርሳ አማካኝነት ልምምዱን በአዳማ አበበ በቂላ ሰርቷል፡፡የዳሽን የተስፋ ቡድን አሰልጣኝ ተገኝ እቁባይ ቡድኑን በጊዜያዊነት ሊረከቡ እንደሚችሉ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን በጊዜያዊነት የተረከቡት አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ ረዳት አሰልጣኝ ሆነው በቅርቡ የተሾሙት አሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው ከሲዳማ ቡና ጋር መለያየታቸው ታውቋል፡፡የአሰልጣኝ ዘላለም ረዳት የነበሩት አለማየሁ አባይነህ በጊዜያዊነት የቡድኑ አሰልጣኝ የሆኑ ሲሆን ትላንት ሲዳማ ቡናን እየመሩ ኤሌከትሪክን 5-0 ማሸነፍ ችለዋል፡፡የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የመልስ ጨዋታ ነገ ጋናን ይገጥማል፡፡ አሰልጣኝ ግርማ ሀብተዮሃንስም ጋናን የሚገጥመው የ18 ተጫዋቾች ስብስብ ይፋ አድርገዋል፡፡አጥቂው ሱራፌል አወል በልምምድ ላይ በደረሰበት ጉዳት ከ18 ተጫዋቾች መካከል አንዱ መሆን አልቻለም፡፡ስብስቡ ይህንን ይመስላል፡-\nምንተስኖት የግሌ ፣ ሚካኤል ለማ ፣ ተክለማርያም ሻንቆ ፣ ተስፋዬ ሽብሩ ፣ ዳዊት ተፈራ ፣ ሃይደር ሙስጠፋ ፣ አሚ መሐመድ ፣ እንየው ካሳሁን ፣ ደስታ ደሙ ፣ ዘላለም ኢሳያስ ፣ ዳዊት ማሞ ፣ ጊት ጋትኮት ፣ ኪዳኔ አሰፋ  ፣ ሃብታሙ ገዛኸኝ ፣ ዘሪሁን ብርሃኑ ፣ ቴዎድሮስ ታፈሰ ፣ አቡበከር ሳኒ ፣ ጀሚል ያዕቆብትላንት በኢትዮጵያ ቡና እና ሀዋሳ ከተማ መካከል የተደረገው ጨዋታ በደጋፊዎች ረብሻ ምክንያት መቋረጡን ተከትሎ የአአ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ መግለጫ አውጥቷል፡፡ኮሚሽኑ በመግለጫው በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰ አያይዞ አጥፊዎችን ለይቶ ለመቅጣት ምርመራ እያደረገ መሆኑንና እርምጃም እንደሚወስድ ጠቅሷል፡፡  ችግሩ እንዳይደገም ከሚመለከተው አካል ጋር እንደሚሰራም አስታውቋል፡፡በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተካሄደ አንድ ጨዋታ ኤሌክትሪክ እቴጌን 1-0 አሸንፏል፡፡\nቅዱስ ጊዮርጊስ 3-1 ኢትዮጵያ ቡና\nደደቢት 3-1 ኢ/ወ/ስ አካዳሚ\nቅዱስ ጊዮርጊስ 1-2 አአ ከተማ", "passage_id": "1df9e5fd90fc5d0c64ecf45b86f2e60e" } ]
092a5b4caa92ecb755a8133ede3bc518
956e9f4278467e5039f6ce84334848ed
በኒውዮርክ ማራቶን ኢትዮጵያውያን ለድል ይጠበቃሉ
ከዓለማችን ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች አንዱ የሆነው የኒውዮርክ ማራቶን ዛሬ ይካሄዳል፡፡ ከሦስት ሳምንት በፊት በዶሃ የዓለም ቻምፒዮና በማራቶን የተሳተፉ በርካታ አትሌቶች በዚህ ውድድር እንደሚሳተፉ ቢጠበቅም ከዓለም ቻምፒዮናው ወዲህ እነዚህ አትሌቶች ለሦስት ወራት ማራቶን እንዳይሮጡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማስጠንቀቁን ተከትሎ ጠንካራ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አይሮጡም፡፡ በዓለም ቻምፒዮናው የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቀው ሌሊሳ ዴሲሳ ያለፈው ዓመት የኒውዮርክ ማራቶን አሸናፊ ሲሆን ይህን ድል ለመድገም ከፍተኛ ግምት የተሰጠው በውድድሩ የማይካፈል አትሌት ነው፡፡ ሌሎች ጠንካራ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ግን ከኬንያውያን ጋር ብርቱ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ በሴቶች መካከል በሚካሄደው ውድድር የ2018 ቻምፒዮኗ ኬንያዊት ማሪ ኪታኒ ትልቅ የአሸናፊነት ግምት አግኝታለች፡፡ 2፡22፡48 በሆነ ሰዓት ሁለተኛውን የውድድር ክብረወሰን ማስመዝገብ የቻለችው ኪታኒ በኒውዮርክ ማራቶን ለአምስተኛ ጊዜ ለማሸነፍ ተዘጋጅታለች፡፡ ኪታኒ ካለፉት አምስት ውድድሮች አራቱን ማሸነፍ ብትችልም ከአስራ ስድስት ዓመት በፊት በማርጋሬት ኦካዮ ተይዞ የቆየውን 2፡22፡31 የሆነ የቦታውን ክብረወሰን ማሻሻል አልቻለችም፡፡ ዘንድሮ ግን ይህን ክብረወሰን ለማሻሻል እንደምትሮጥ አሳውቃለች፡፡ ባለፉት አራት ውድድሮች ሁለተኛ ሆና ማጠናቀቅ የቻለችው ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሩቲ አጋ ኪታኒን የማሸነፍ ግምት ቢሰጣትም በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በመሳተፏ ኒውዮርክ ላይ ተፎካካሪ ላትሆን ትችላለች፡፡ ያም ሆኖ ባለፈው ሁስተን ማራቶን ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው በላይነሽ ፍቃዱ ጠንካራ ፉክክር ታደርጋለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በላይነሽ በማራቶን 2፡26፡41 የሆነ የግሏ ፈጣን ሰዓት አላት፡፡ 2፡28፡06 ሰዓት ያላት ቡዜ ድሪባ ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብለው ከሚጠበቁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መካከል አንዷ ነች፡፡ በወንዶች መካከል በሚካሄደው ውድድር የዓለም ቻምፒዮኑ ሌሊሳ ዴሲሳ ተሳታፊ ባይሆንም ባለፈው ዓመት በኒውዮርክ ማራቶን ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ሹራ ቂጣታ ከፍተኛ የአሸናፊነት ግምት ተሰጥቶታል፡፡ እስካሁን አስራ አንድ የማራቶን ውድድሮችን ያደረገው ሹራ ብዙ የአሸናፊነት ታሪክ ባይኖረውም ገና ሃያ ሦስተኛ ዓመቱ ላይ የሚገኝ መሆኑ ወደ አሸናፊነት ሊመጣ እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ታምራት ቶላ የዚህ ውድድር አሸናፊ የመሆን አቅም እንዳለው እየተነገረ ነው፡፡ የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ አሸናፊው ታምራት 2017 ላይ በዱባይ ማራቶን ካሸነፈ ወዲህ በጥሩ አቋም ላይ ባይገኝም በማራቶን ጥሩ አቅም ያለው አትሌት ነው፡፡ ባለፈው ሚያዝያ በለንደን ማራቶን ስድስተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ታምራት ባለፈው ቦጎታ ማራቶን አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል፡፡ኬንያዊው አትሌት ጂኦፍሪ ኮምዎረር በዛሬው ውድድር ትኩረት የሚሰጠው ነው፡፡ በርካታ የግማሽ ማራቶን ድሎችን በማጣጣም የሚታወቀው ኮምዎረር በማራቶን ትልቅ ስም ባይኖረውም ዛሬ ለኢትዮጵያውያኑ ፈተና እንደሚሆን እምነት ተጥሎበታል፡፡አዲስ ዘመን ጥቅምት23/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=21918
[ { "passage": " በዓለም ከምርጦቹ የጎዳና ላይ ሩጫዎች መካከል አንዱ በመባል እውቅና ያገኘውና በአፍሪካ ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር የሆነው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ፣ በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ተወዳጅና ተናፋቂም ነው። በሯጮቹ ምድር ከዓመት ዓመት እየደመቀና ዝነኝነቱም እያደገ የመጣው ዓመታዊው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ትናንት ለ19 ጊዜ ‹‹ሴቶች ልጆች በእኩል ሚዛን መታየት ፤ መደመጥና ተቀባይነት ሊኖራቸው ይገባል›› በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል።ከተሳታፊው 45ሺ ሰው ባሻገር 500 የሚሆኑ የውጪ ሃገር ዜጎችም በዚህ ውድድር ላይ ታድመዋል። 22 የሚሆኑ ድርጅቶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም የውጪ ሃገራት ዝነኛ የመገናኛ ብዙኃንም በሩጫው ላይ ተገኝተው ሽፋን ሰጥተዋል። በሩጫው ላይ 500 የሚሆኑ አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ ከኢትዮጵያዊያኑ ጎን ለጎን የኬንያ፣ የቦትስዋና፣ ኤርትራ እና ዩጋንዳ አትሌቶችም ተካፋይ ሆነዋል። ከተሳታፊ አትሌቶች ባሻገር ከዚህ ቀደም በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያሸነፉ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ውድድሮች ተሳታፊና ታዋቂ የሆኑ አትሌቶች ትናንትም ሮጠዋል። ከእነዚህ መካከል አንዱአምላክ በሪሁ፣ አብ ጋሻሁን፣ ሞገስ ጥኡማይ፣ ፎትን ተስፋዬ፣ ያለምዘርፍ የኋላ፣ ሹሬ ደምሴ እና አበሩ ዘውዴ ጥቂቶቹ ናቸው። የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ ኢትዮጵያዊያኑ ብርቅዬዎችና የዓለም ቻምፒዮናዎቹ ኃይሌ ገብረስላሴ፣ ገዛኸኝ አበራ፣ ሌሊሳ ዴሲሳ፣ ብርሃኔ አደሬ፣ መሰረት ደፋር፣ ሰለሞን ባረጋ እንዲሁም በ5ሺ ሜትር የዓለም ቻምፒዮናዋ ኬንያዊት አትሌት ሄለን ኦቤሪ ደግሞ ሩጫውን ያስጀመሩ የክብር እንግዶች ነበሩ። ፖስታ ቤት አካባቢ ካለው መነሻ በቅድሚያ የተነሱት ወንድ አትሌቶች መካከል ከፍተኛ ፉክክር የታየ ሲሆን በማይክሮ ሰከንድ ልዩነትም የሱር ኮንስትራክሽን አትሌቱ በሪሁ አረጋዊ አንደኛ በመሆን የ2012 ዓም የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ቻምፒዮን ሆኗል። አትሌቱ የገባበት ሰዓት 28፡22.180 ሲሆን፤ በዶሃ የዓለም ቻምፒዮና በአስር ሺ ሜትር ጠንካራ ተፎካካሪ የነበረው አትሌት አንዱአምላክ በልሁ በማይክሮ ሰከንዶች ተቀድሞ 28፡22.181 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ሆኖ ውድድሩን ፈጽሟል። የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ክለብ አትሌቱ ገመቹ ዲዳ ደግሞ የገባበት 28፡46.438 የሆነ ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዞ እንዲፈፅም አድርጎታል።አሸናፊው በሪሁ ከሩጫው በኋላ በሰጠው አስተያየትም ጠንካራ ፉክክር በነበረው ሩጫ አሸናፊ በመሆኑ ደስተኛነቱን ገልጿል። ከዚህ ቀደም አሸናፊ ባይሆንም በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተሳታፊ የነበረው በሪሁ፤ ያለፈውን ዓመት በጉዳት በማሳለፉ በዚህ ውድድር እንዲሁም በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና መሳተፍ አለመቻሉንም ተናግሯል። ከጉዳት ካገገመ በኋላም በዚህ ውድድር ከአንድ እስከ ሦስት ያለውን ደረጃ በመያዝ ለማጠናቀቅ ልምምዱን ሲያደርግ ቆይቷል። ከፍተኛ ፉክክር በተካሄደበት ሩጫ ግን በጠባብ የሰዓት ልዩነት አሸናፊ ሆኗል። ከዚህ በኋላም ጠንክሮ በመስራት በቅርቡ ለሚካሄደው 2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ ሃገሩን የመወከል ፍላጎት እንዳለው ጠቁሟል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በአገር ውስጥም ይሁን በዓለም አቀፍ ውድድሮች የመታየት እድል ያላገኙ አዳዲስ ቻምፒዮኖች ብቅ የሚሉበት ዓለም ነው። በዚህ ውድድር አሸንፈው ለታላቅ ስኬት የበቁ አትሌቶችም በርካታ ናቸው። ምክኒያቱም ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ላይ ያሸነፉ ብቻም ሳይሆን ጠንካራ ተፎካካሪ የሆኑ አትሌቶች በማኔጀሮች የመታየት እድላቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። የዘንድሮ ቻምፒዮን በሪሁም የውድድሩ አዲስ ቻምፒዮንና ወደ ፊት ተስፋ የሚጣልበት አትሌት እንደሚሆን ተፎካካሪዎቹ የነበሩትን አትሌቶች አቅም ከግምት አስገብቶ መተንበይ ይቻላል። ከሁለት ሰከንድ በኋላ በተጀመረው የሴቶች ምድብ በኩል አሸናፊ የሆነችው የግሎባል ስፖርት አትሌቷ ያለምዘርፍ የኋላው ስትሆን፤ 31፡54.000 የገባችበት ሰዓት ነው። የትግራይ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን የወከለችው ትዕግስት ገብረሰላማ እና የግል ተሳታፊዋ አለም ንጉስ ደግሞ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ሆነዋል። 32፡20.000 እና 32፡23.000 አትሌቶቹ የገቡበት ሰዓት ሆኖ ተመዝግቧል። በሁለቱም ጾታ አሸናፊ የሆኑት አትሌቶችም ከሜዳሊያ እና ከዋንጫ ሽልማታቸው ባሻገር 100ሺ፣ 30ሺ እና 20ሺ ብር ተበርክቶላቸዋል። አዲስ ዘመን ኅዳር 8/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "d5a5c42fe0e630f4adac361bfb3fbf8e" }, { "passage": " በሳምንቱ የዕረፍት ቀናት በተካሄዱ በርካታ ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች እንደተለመደው የድል ባለቤቶች ሆነዋል። በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ በተሰጠው የፍራንክፈርት ማራቶን ፍቅሬ ተፈራ አሸናፊ ሆኗል። አትሌቱ የበላይነቱን የያዘው 2:07:08 በሆነ ሰዓት ሲሆን፤ በሁለት ሰከንዶች የዘገየው ዳዊት ወልዴ ደግሞ ሁለተኛ ሆኗል። ለባህሬን የሚሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊው አወቀ ይመር በሦስተኛነት ማጠናቀቅ ችሏል። በሴቶች በኩልም የቦታው ክብረወሰን በኬንያዊቷ አትሌት ተሻሽሏል፤ ቫለሪ አያቢ ያጠናቀቀችበት ይህ 2:19:10 የሆነ ሰዓት በዓለም የምንጊዜም 12ኛው ፈጣን ሰዓት ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ መገርቱ ከበደ እና መስከረም አሰፋ ደግሞ በጠባብ ደቂቃዎች ልዩነት ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ቫሌንሲያ ግማሽ ማራቶን የወርቅ ደረጃ ባለው በዚህ ውድድርም ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸናፊዎች ሆነዋል። በዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና በ3ሺ ሜትር የክብረወሰን ባለቤቱ የሆነው ዮሚፍ ቀጄልቻ 59:05 በሆነ ሰዓት የመጨረሻዋን መስመር አቋርጧል። ዮሚፍ በቅርቡ በተጠናቀቀው የዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በ10ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በሁለት ሰከንድ የዘገየው ኬንያዊው በናርድ ኔጌኖ ሁለተኛ ሲሆን፤ ጀማል ይመር ሶስተኛ በመሆን አጠናቋል፡፡ በሴቶች በኩል አሸናፊዋ አትሌት ሰምበሬ ተፈሪ 1:05:32 የሆነ ሰዓት ስታስመዘግብ ሰዓቷ የኢትዮጵያ ክብረወሰን ሆኗል፡፡ በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና የ10ሺና 1500 ሜትር ቻምፒዮን የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ\nየኔዘርላንድስ አትሌት ሲፋን ሃሰን በ21 ሰኮንዶች ዘግይታ  በመግባት\nሁለተኛ ሁናለች።ኬንያዊቷ ጆዋን ቼሊሞ ደግሞ እነርሱን በመከተል በሶስተኝነት ያጠናቀቀች አትሌት ናት። ስሎቫንያ ማራቶን በዚህ ማራቶን ከልክሌ ገዛኸኝ ኬንያዊያኑን አትሌቶች በማስከተል አሸናፊ ሆኗል። አትሌቱ የገባበት ሰዓት 2:07:29 ሲሆን፤ አንቶኒ ኪፕላጋት ማርቲም እና ቪንሰንት ሮኖ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል። በሴቶች መካከል በተከናወነው ውድድርም ኬንያዊቷ ቦርነስ ቺፕኪሩይ ኪቱር 2:21:26 በሆነ ሰዓት የቦታውን ክብረወሰን አሻሽላለች። በዚህ ውድድር አምስት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከአራተኛ እስከ አስረኛ ባሉት ደረጃዎች ውድድራቸውን ጨርሰዋል። ሃዋይ ማራቶን በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የነሃስ ደረጃ በተሰጠው በዚህ ውድድር ሌንጮ አንበሳ፣ ሄነሪ ኪፕሮፕ እና አንድሬው ኪሚታይ እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል፡፡ በሴቶች በኩልም ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዋቄ መቃ ሁለት ኬንያዊያን አትሌቶች ተከትላ በመግባት በሶስተኛነት ውድድሩን ፈፅማለች፡፡ ቻንግሻ ኢንተርናሽናል ማራቶን\nየነሃስ ደረጃ ባለውና በብርዳማ የአየር ሁኔታ በተካሄደው በዚህ ውድድር አብዲ ከበደ፤ በቦታው የተያዘውን ክብረወሰን በ50 ሰከንድ በማሻሻል 2:10:23 በሆነ ሰዓት ገብቷል። ኬንያዊው ዴቪድ ኪፕሮኖ እና ኢትዮጵያዊው ወርቅነህ ተስፋም ከቀደመው ክብረወሰን በፈጠነ ሰዓት ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ማርሴል 20 ኪሎ ሜትር በፈረንሳይ ማርሴል ሃያ ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ኢትዮጵያዊው ኦሊካ አዱኛ አሸናፊ ሆኗል፡ ፡ ከአስር ዓመታት ወዲህም በውድድሩ በተከታታይ ሁለት ዓመታት ማሸነፍ የቻለ አትሌት ሆኗል፡፡ ኦሊካ ውድድሩን በ1:01:10, 41 ሲፈፅም ኬንያዊው ኪፕሮኖ ሜንጆ 1:01:50 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ፣ ኮሪር ኪፕየጎን በ1:02:13 ሦስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል፡፡ ሰንበሬ ተፈሪ የኢትዮጵያን የግማሽ ማራቶን ክብረወሰን በ1:05:32\nሰዓት አስመዝግባለች፣አዲስ ዘመን ጥቅምት 18/2012 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "c4fc27a94a3fe24850ed23b3927e7d03" }, { "passage": " በተለያዩ የዓለም ከተሞች በመዘዋወር የሚካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር፤ ዘጠነኛውን ዙር በሞናኮ ያካሂዳል። በተያዘው ሳምንት መጨረሻ በዕለተ አርብ የሚካሄደው ይህ ውድድር፤ ዘንድሮ መታሰቢያነቱን ለአንድ አትሌት አድርጓል። በቅርቡ በሞት የተለየችውን በ1ሺ 500 ሜትር እና 5ሺ ሜትር ሩጫዎች ታዋቂዋን አሜሪካዊት አትሌት ጋብሬሌ ግሩንዋልድ። ባለፈው ወር በካንሰር ህመም ለህልፈት የተዳረገችው አትሌቷ፤ በተያዘው ወር 33ኛ ዓመት የልደት በዓሏን ታከብር ነበር። ይህንን እና አትሌቷ እአአ በ2013 በ1ሺ500 ሜትር የግሏን ምርጥ ሰዓት ማስመዝገቧን ምክንያት በማድረግ ሩጫው መታሰቢያ እንዲሆናት መደረጉን ዳይመንድ ሊግ በድረገጹ አስነብቧል። ከዚህ ባሻገር በሴቶች መካከል የሚካሄደው የማይል ውድድር የጋቤ ማይል በሚል ተሰይሟል። ይህ ውድድርም ሦስት ሴት የዓለም ክብረወሰን ባለቤት አትሌቶችን የሚያገናኝ ሲሆን፤ እአአ በ2015 የ1ሺ500 ሜትር ውድድር ክብረወሰን የሰበረችው ገንዘቤ ዲባባን፣ ያለፈው ዓመት የ3ሺ ሜትር መሰናክል ባለ ክብረወሰኗ ባትሬስ ቼፕኮች እንዲሁም በዚህ ዓመት የ5ኪሎ ሜትር ክብርን የተቀዳጀችው ሲፈን ሃሰን የሚያደርጉት ፍልሚያ ተጠባቂ ሆኗል። ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ደግሞ በርቀቱ የሴቶች ቁጥር አንድ አትሌት በመሆኗ ለአሸናፊነት ትጠበቃለች። ገንዘቤ እአአ በ2015 በሞናኮ ርቀቱን ያሸነፈችበት 3:50:07 የሆነ ሰዓት እስካሁንም ሊደፈር ያልቻለ የዓለም ፈጣኑ ሰዓት ሲሆን፤ አትሌቷ የዓለም ሻምፒዮናም ነበረች። በዓለም ሻምፒዮናው በ5ሺ ሜትርም ሜዳሊያ ያጠለቀችው አትሌቷ የዓመቱ ምርጥ ሴት አትሌት በሚል መመረጧም የሚታወስ ነው። በቤጂንጉ ዓለም ሻምፒዮና ሻምፒዮን ስትሆንም በሪዮ ኦሊምፒክ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። ከዚህ ባሻገር በዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የ1ሺ500 ሜትር ለንግስናዋ ተስተካካይ አልተገኘላትም። የርቀቱን ክብረወሰን የጨበጠችበት የዚህ ርቀት ሰዓት የተመዘገበው በሞናኮ መሆኑ እንዲሁም በርቀቱ ያላት ልምድ ደግሞ በዚህ ውድድር ላይም አግዟት እንደምታሸንፍ በአትሌቲክስ ቤተሰቡ ዘንድ ተስፋ ተጥሏል። በዚህ ርቀት ታዋቂ የሆነችውና በቤጂንግ እና የለንደን የአትሌቲክስ ዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ ሁለት የነሐስ ሜዳሊያዎችን ማጥለቅ ችላለች። አትሌቷ በተለያዩ አህጉር አቀፍ ውድድሮችና ሌሎች ውድድሮች ላይም በ1ሺ 500ሜትር የተሻለ ውጤት ካስመዘገቡ አትሌቶች መካከል ትጠቀሳለች። አትሌቷ ከወራት በፊት በዚሁ በሞናኮ በተካሄደ የ5ኪሎ ሜትር ሩጫ ላይ14:44 የሆነ ክብረወሰን አስመዝግባለች። አትሌቷ የርቀቱን የመጨረሻ መስመር የረገጠችበት ሰዓት ክብረወሰን ሊባል የቻለው 15:48 የነበረውን የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻሉ ነው። ይህም ሲፈንን ለባለ ክብረወሰኗ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ፈተና እንደሚሆንባት ይጠበቃል። ኬንያዊቷ አትሌት የመሰናክል ስፔሻሊስት የምትባል ሲሆን፤ በሪዮ ኦሊምፒክና በለንደኑ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናዎች ላይ አራተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። ከዚያ በኋላ ባሉት ጊዜያት ግን በርቀቱ ወደ አሸናፊነት ከመምጣትም ባለፈ የክብረወሰን ባለቤት ልትሆን ችላለች። ርቀቱን 8:50 የነበረውን ሰዓት 8:45 በማሻሻል የመጀመሪያዋ ሴት አትሌት ናት። አትሌቷ ከመሰናክል ባሻገር በ1ሺ500 ሜትርም የምትሮጥ ሲሆን፤ እአአ በ2015 በተሳተፈችበት የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤት ነበረች። ባለፈው ዓመት በተካሄደው የኮመን ዌልዝ ጌምስ ርቀቱን ሁለተኛ በመውጣት ርቀቱን ሸፍናለች። በዚያው ዓመት በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ተሳትፎዋም ሰባተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። ይህ ውጤቷም አትሌቷን በዚህ ርቀት የተሻለ ውጤት ታመጣለች በሚል እንድትጠበቅ አድርጓታል። በወንዶች በኩል ደግሞ በቅርቡ ለረጅም ዓመታት ተይዞ የቆየውን ክብረወሰን መስበር የቻለው ወጣቱ አትሌት ሳሙኤል ተፈራ ተሳታፊ እንደሚሆን ታውቋል። በዚህ ውድድርም በተመሳሳይ ጠንካራ አትሌቶች የሚሳተፉበት እንደመሆኑ የአሸናፊነት ግምቱ አዳጋች ሆኗል። ኢትዮጵያዊው አትሌት በቅርቡ በበርሚንግሃም በተካሄደው የቤት ውስጥ የዓለም ሻምፒዮና፤ 1ሺ500 ሜትሩን ለመሸፈን የፈጀበት ጊዜ 3:31.04 ነበር። ይህም በውድድሩ አሸናፊ ይሆናል በሚል እንዲጠበቅ ቢያደርገውም፤ የዓለም ሻምፒዮኑ ኤልጃህ ማናንጎይ እና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኑ ማቲው ሴንትሮዊትዝ ለውድድሩ ከባድ ፈተና እንደሚሆኑ ተገምቷል።አዲስ ዘመን ሀምሌ 1/2011 ", "passage_id": "4c4d78e5ad8be6855a25b83661664340" }, { "passage": "የዓለማችን ታላላቅ ከተሞች በየዓመቱ ከሚያ ስተናግዷቸው በርካታ የማራቶን ውድድሮች በሚያፎካክራቸው አትሌቶች ደረጃና ጥራት ቀዳሚ ሆኖ የሚገኘው የለንደን ማራቶን ነው። ይህ ውድድር የፊታችን እሁድ ሲካሄድ እንደተለመደው በርቀቱ ስመ ጥር የሆኑ በርካታ አትሌቶችን በሁለቱም ፆታ ለማፎካከር ተዘጋጅቷል። ባለፉት ሦስት ዓመታት በኬንያዊው የርቀቱ ፈርጥና የዓለም ክብረወሰን ባለቤት ኢሉድ ኪፕቾጌ የበላይነት ተይዞ የቆየው የለንደን ማራቶን ዘንድሮ በአገሩና በደጋፊው ፊት በሚሮጠው ሞሐመድ ፋራህ ይደምቃል ተብሎ ይጠበቃል። የዘንድሮው ውድድር በሦስት ጊዜ ባለ ድሉ ኪፕቾጌና በፋራህ መካከል የሚደረገው ፉክክር ከወዲሁ ትኩረት ቢያገኝም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርቀቱ አስደናቂ ብቃት እያሳዩ በሚገኙት ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ሹራ ቂጣታ፣ ሞስነት ገረመውና ልዑል ገብረሥላሴ የበለጠ እንደሚደምቅ ይጠበቃል። በሁለት ኦሊምፒኮችና በሦስት የዓለም ቻምፒዮናዎች የአምስትና አስር ሺ ሜትር ንጉሥ ሆኖ መዝለቅ የቻለው ሞ ፋራህ ካለፈው ዓመት ወዲህ ፊቱን ወደ ማራቶን መመለሱ ይታወቃል። ባለፈው የለንደን ማራቶን ሦስተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ፋራህ ጥቅምት ወር ላይ በቺካጎ ማራቶን በ2:05:11 የአውሮፓን ክብረወሰን አስመዝግቦ የመጀመሪያ ድሉን ካጣጣመ ወዲህ የዓለማችን የወቅቱ ኮከብ የማራቶን አትሌቶችን ጎራ ተቀላቅሏል። ድንቅ የማራቶን አትሌት መሆኑን ለማወጅም የእንግሊዝ መገናኛ ብዙኃን የእሁዱን የለንደን ማራቶን ድል አሰፍስፈው እየጠበቁ ይገኛሉ። ጥያቄው ግን ሌላው ይቅርና ፋራህ ኪፕቾጌን ማቆም እንዴት ይቻለዋል ነው? አንዳንድ የአገሬው መገናኛ ብዙኃን ኪፕቾጌ ምንም ያህል የርቀቱ ኮከብና ባለ ክብረወሰን ቢሆን ከእድሜው መግፋት ጋር ተያይዞ አንድ ቀን እጅ እንደሚሰጥ እርግጠኛ ሆነዋል። ያም ቀን የፊታችን እሁድ ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን እያስቀመጡ ነው። ያም ሆኖ ኪፕቾጌ አሁን ያለው አቋም ካለፈው ዓመት አኳያ የተሻለ እንጂ የባሰ እንደማይሆን ከልምምዶቹ መረዳት ይቻላል። ኪፕቾጌ ባለፈው ዓመት ወደ ተመሳሳይ ውድድር ከመምጣቱ በፊት በተለያዩ ውድድሮች ማራቶንን ከ2፡00 በታች ለማጠናቀቅ ብዙ ጥረት አድርጎ ነበር። ይህም ከአቅሙ በላይ ጉልበቱን እንዲያሟጥጥ አድርጎታል በሚል የለንደን ማራቶንን እንደማያሸንፍ ተጠርጥሮ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ድንቅ ኬንያዊ ለሦስተኛ ጊዜ ለንደን ላይ ነግሷል። ከዚያም ባለፈ ባለፈው የበርሊን ማራቶን 2:01:39 የሆነውን የዓለም ክብረወሰን በአስደናቂ ብቃት የግሉ ማድረግ ችሏል። ኪፕቾጌ በርሊን ላይ ያስመዘገበው ክብረሰወን የብቃቱ ጥግ ነው። ይህን ብቃቱን ዘንድሮ ላይደግመው ቢችል እንኳን ባለፉት ሦስት የለንደን ማራቶኖች ሲያሸንፍ ያስመዘገባቸው ሰዓቶች በአማካኝ ሲሰሉ 2:04:01 ነው። ታዲያ ፋራህም ይሁን ሌሎቹ ጠንካራ ተፎካካሪዎች ይህን እንዴት መመከት ይቻላቸዋል የሚሉ የስፖርቱ ቤተሰቦች በርካታ ናቸው። ኪፕቾጌ የዓለም ክብረወሰን የሆነውን ሰዓት ማስመዝገብ የቻለው በሂደት እየበሰለ መጥቶ በአስራ አንደኛው የማራቶን ውድድሩ ነው። እድሜው ሰላሳ አራት ሲሆን ሞ ፋራህን በሁለት ዓመት ብቻ ይበልጠዋል። ፋራህ እንደ ቀደምቶቹ ኮከብ አትሌቶች ወደ ማራቶን የመጣው በርካታ ዓመታትን በመም ውድድሮች አልፎ መሆኑ በማራቶን ጥሩ አትሌት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ባለፈው ዓመት በመጀመሪያ የማራቶን ውድድሩም ሦስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ የነበረው በራስ መተማመንና በልምድ የሚበልጡትን የስነ ልቦና ጫና መቋቋም መቻሉ ዘንድሮ የተሻለ ነገር እንዲያሳይ ይረዳዋል የሚል መደምደሚያ ላይ አድርሷል። ሁለቱ ታላላቅ አትሌቶች ቀድመው ከገነቡት ስም አኳያ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን በፉክክሩ ግንባር ቀደም ሆነው ይጠቀሱ እንጂ ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ያልተገመተ ነገር ሊፈጥሩ እንደሚችሉ መጠበቅ ያስፈልጋል። በተለይም ባለፈው ዓመት በዚሁ ውድድር ኪፕቾጌን ተከትሎ ሁለተኛ በመሆን ያጠናቀቀው ሹራ ቂጣታ ፋራህን በ1፡ 32 ሰከንድ ልዩነት ቀድሞ መግባቱ ሊሰመርበት ይገባል። በሌላ በኩል ባለፈው የዱባይ ማራቶን የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል ያሸነፋው ሞስነት ገረመው ፋራህ በቺካጎ ማራቶን ሲያሸንፍ በአስራ ሦስት ሰከንዶች ዘግይቶ ሁለተኛ ማጠናቀቁ በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ሌላኛው ትኩረት የሚሰጠው ኢትዮጵያዊ ልዑል ገብረሥላሴ ባለፈው ዓመት ማራቶንን ከ2፡05 በታች ማጠናቀቅ ከቻሉ ሦስት አትሌቶች አንዱ እንደመሆኑ ቀላል ተፎካካሪ አይሆንም። ይህ አትሌት በዱባይ ማራቶን 2፡ 04፡02 ያስመዘገበ ሲሆን ቫሌንሲያ ላይ 2፡04፡ 31 በሆነ ሰዓት የቦታውን ክብረወሰን ማሻሻል ችሏል። ስለዚህ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ከፋራህ ይልቅ ለኪፕቾጌ አስፈሪ ሊሆኑ የሚችሉት ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ናቸው። እንደ ዘንድሮው የለንደን ማራቶን የትኛውም የማራቶን ውድድር በሴቶች ድንቅ የሆነ ፉክክር እንደማይታይ ከወዲሁ እየተነገረ ነው። በሴቶች መካከል ተፎካካሪ የሚሆኑት አትሌቶች ባለፈው ጥር ይፋ ሲደረጉ ከ2018 የወርልድ ማራቶን ሜጀርስ (WMM) ስድስት አሸናፊዎች አምስቱ መካተታቸው ጉድ ተብሎለት ነበር። ከነዚህ በተጨማሪ የ2018 የዱባይ ማራቶን ቻምፒዮንና በታሪክ በርቀቱ ፈጣን ከሆኑት አምስት አትሌቶች አራቱ መካተታቸው የዘንድሮውን የለንደን ማራቶን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ተጠባቂ አድርጎታል። ከዚያን ጊዜ ወዲህ ግን የተቀየሩ ነገሮች መኖራቸው አልቀረም። የረጅም ርቀት ንግስቷ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ሁለተኛ ልጇን እንደ ፀነሰች መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ የዘንድሮው የለንደን ማራቶን የሴቶች ፉክክር ላይ ቀድሞ የነበረው አሰላለፍ እንደሚቀየር ይጠበቃል። ቀደም ሲል የዓለማችን ሁለተኛ፣ ሦስተኛ፣ አራተኛና አምስተኛ ፈጣን ሰዓት ባለቤት የሆኑ አትሌቶች እንደሚፎካከሩበት የተነገረው ውድድር አሁን ሁለተኛ፣ ስድስተኛ፣ ሰባተኛና ዘጠነኛ ፈጣን ሰዓት ያላቸው አትሌቶች የሚፎካከሩበት ሆኗል። የሦስት ጊዜ የለንደን ማራቶንና የአራት ጊዜ የኒውዮርክ ማራቶን አሸናፊዋ ኬንያዊት ማሪ ኪታኒ የዘመኗ ምርጥ አትሌት ነች። ይህም በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ቀዳሚ የትኩረት ማረፊያ አድርጓታል። የኦሊምፒክ 5ሺ ሜትር ቻምፒዮኗ ቪቪያን ቼሪዮት ያለፈው ለንደን ማራቶን አሸናፊና የኒውዮርክ ማራቶንን ሁለተኛ ሆና ያጠናቀቀች አትሌት መሆኗ በሁለተኛነት ትኩረት አሰጥቷታል። 2:18:11 በሆነ ሰዓት የበርሊን ማራቶንን ክብረወሰን የጨበጠችው ግላዲ ቺሮኖ ትልቅ ትኩረት ያገኘች ሌላኛዋ ኬንያዊት ነች። እነዚህ ግዙፍ ስም ያላቸው ኬንያውያን ከእነሱ እኩል አቅም ያላቸውን የዘወትር ተፎካካሪ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚፎካከሩበት ውድድር አጓጊ ባይሆን ይገርማል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማራቶን ጎልቶ የሚጠራ የኢትዮጵያውያን ስም መካከል ሮዛ ደረጄ አንዷ ናት። 2:19:17 በሆነ ሰዓት ባለፈው ዓመት የዱባይ ማራቶን ክብረወሰንን ሰብራለች። ባለፈው የካቲት ደግሞ በባርሴሎና ግማሽ ማራቶን 66፡01 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችላለች። ሮዛ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን ለኬንያውያን ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል። ባለፈው ቶኪዮ ማራቶን 2:19:51በሆነ ሰዓት ስታሸንፍ የቦታውን ክብረወሰን በአራት ሰከንዶች ከማሻሻል የቀረችው ብርሃኔ ዲባባ በእሁዱ ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ እንደምትሆን ትጠበቃለች።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 17/2011 ", "passage_id": "f9e47a6c3e9aba6b3a6876efad7b1929" }, { "passage": " ውድድር ዓመቱ የዳይመንድ ሊግ ፉክክሮች እየተጋመሱ መጥተው የአሜሪካዋ ዩጂን ከተማ ደርሰዋል፡፡ ዩጂን ዛሬ በተለያዩ ርቀቶች በርካታ ፉክክሮችን ስታስተናግድ በሴቶች መካከል የሚካሄደው የሦስት ሺ ሜትር ውድድር ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ሆኗል፡፡ የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮኗ ኢትዮጵያዊት አትሌት አልማዝ አያና\nከረጅም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር ተመልሳ የመጀመሪያ ፉክክሯን ዩጂን ላይ ታደርጋለች፡፡ አልማዝ ወደ ውድድር መመለሷ ለፉክክሩ ድምቀት የሰጠው ሲሆን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ ምድር በርካታ የዓለማችን ድንቅ አትሌቶች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ታውቋል፡፡ ከነዚህም መካከል አልማዝን ጨምሮ ገንዘቤ ዲባባ፣ሔለን ኦቢሪ፣ሲፈን ሃሰን፣ካስተር ሲሜንያና ሌሎችም ድንቅ የመካከለኛና የረጅም ርቀት አትሌቶች ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ይጠበቃል። በውድድር ዓመቱ\nአምስት ሺ ሜትርን በበላይነት ተቆጣጥራ የያዘችው ኬንያዊቷ ኮከብ አትሌት ሔለን ኦቢሪ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ በዩጂን አጠናክራ እንደምትቀጥል ይጠበቃል። የሃያ\nዘጠኝ ዓመቷ ኦቢሪ የዓለም ቻምፒዮን ከመሆኗ ባሻገር በዘንድሮው ዓመት በአገር አቋራጭ ቻምፒዮና ወርቅ ማጥለቅ ችላለች፡፡ ባለፈው ሪዮ ኦሊምፒክ የብር ሜዳሊያ ካጠለቀች ወዲህም በለንደን አትሌቲክስ ቻምፒዮና ወርቅ ማጥለቋ ይታወሳል። ከ1500 ሜትር\nሯጭነት ተነስታ በረጅም ርቀት ኮከብ አትሌት መሆን የቻለችው ኦቢሪ እኤአ 2013 ላይ በዚሁ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ድንቅ ብቃት አሳይታለች፡፡ 2014 ላይም በአሜሪካ ምድር የምን ጊዜም ፈጣን ሰዓት የሆነውን 3፡57፡05\nማስመዝገቧ በዛሬው ውድድር ከፍተኛ የአሸናፊነት ግምት እንዲሰጣት አድርጓል፡፡ ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን 2015 ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የዳመንድ ሊግ ውድድር አሸናፊ መሆኗ የሚታወስ ሲሆን በ2016 አሜሪካ ፖርትላንድ የቤት\nውስጥ የዓለም ቻምፒዮና ወርቅ ማጥለቅ ችላለች፡፡ ሲፈን ያለፈውን የ2017 ውድድር ዓመትን በተለያዩ ሦስት\nርቀቶች ከምርጥ አምስት አትሌቶች ውስጥ መካተት ችላለች። ከ8 መቶ\nሜትር እስከ 5 ኪሎ ሜትር ድንቅ ብቃት ማሳየት የቻለችው ሲፈን ባለፈው የውድድር ዓመት በ5ኪሎ\nሜትር ሁለተኛና በ1500 ሜትር\nሦስተኛ ሆና ማጠናቀቅ ችላለች፡፡ ዘንድሮም ሲፈን በድንቅ አቋም ላይ የምትገኝ አትሌት መሆኗ በዩጂን ለአሸናፊነት ከሚጠበቁ አትሌቶች አንዷ ለመሆን በቅታለች፡፡ ከፆታዊ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ውዝግብ ውስጥ የምትገኘው ደቡብ አፍሪካዊት ካስተር ሲሜንያ በዩጂን ዳይመንድ ሊግ መካተቷ ውድድሩን በተወሰነ ደረጃውን ከፍ እንዲል አድርጓታል፡፡ የሁለት ኦሊምፒክና ሦስት የዓለም ቻምፒዮና አሸናፊዋ ሲሜንያ በ8መቶ\nሜትር ለሰላሳኛ ጊዜ ያለመሸነፍ ጉዞዋን ማስጠበቅ በመቻሏ አድናቆትን አትርፋለች። ከለመደችው የመወዳደሪያ ርቀት ከፍ ብላ በሦስት ሺ ሜትር\nየምታደርገውን ፉክክርም በተደጋጋሚ ማሸነፍ እንደምትችል ማሳየቷን ተከትሎ ለርቀቱ ኮከቦች ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡ የ28 ዓመቷ ድንቅ የመካከለኛና ረጅም ርቀት አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ከሰባት በላይ የዓለም ክብረወሰኖችን መያዝ የቻለች ሲሆን በዩጂን ባለፉት ሦስት የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች የተፎካከረችው በ5 ሺ\nሜትር ነው፡፡ በተለይም 2015 ላይ በዚሁ በ5ሺ\nሜትር 14:19.76 በመሮጥ በአሜሪካ ምድር የምንጊዜም ፈጣን ሰዓት ማስመዝገብ ችላለች። ገንዘቤ ባለፈው ዓመት በዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና በ1500ና\n3 ሺ ሜትር ጥምር ወርቅ በማጥለቅ የመጀመሪያዋ የዓለማችን አትሌት መሆን ችላለች። በዘንድሮው ዓመት 1500 ሜትርን 359፡08 አስመዝግባ ማሸነፍ የቻለች ሲሆን\nበ3 ሺ ሜትር ደግሞ በዶሃ ዳይመንድ ሊግ ኬንያዊቷ ኦቢሪን ተከትላ 8:26.20 ሰዓት ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ከጉዳት ተመልሳ የመጀመሪያ ውድድሯን የምታደርገው አልማዝ በሪዮ ኦሊምፒክ 10ሺ ሜትርን 29፡17፡45 በሆነ የዓለም ክብረወሰን ሰዓት ማሸነፏ የሚታወስ ሲሆን 2016 ላይ የ5ሺ\nሜትር የዳይመንድ ሊጉ አጠቃላይ አሸናፊ ነበረች። በ2015 የቤጂንግ የዓለም ቻምፒዮና የውድድሩን ክብረወሰን በማሻሻል በ5ሺ ሜትር ስታሸንፍ በ2017 የዓለም ቻምፒዮና በ10ሺ ሜትር ወርቅ ማጥለቋ አይዘነጋም፡፡ ካለፈው አንድ ዓመት በላይ ግን አልማዝ በጉዳት ከውድድር ርቃ ቆይታለች። ይህም በክረምቱ መጨረሻ ኳታር ለምታዘጋጀው የዓለም ቻምፒዮና አትደርስም የሚል ስጋት ፈጥሮ ነበር፡፡ አልማዝ አሁን ልምምዷን በተገቢ ሁኔታ እያከናወነች ሲሆን የዩጂን ዳይመንድ ሊግም ድንቅ ብቃቷን ታሳይበታለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በ2015 የቤጂንግ የዓለም ቻምፒዮና የ5ሺ\nሜትር ውድድር በበርካቶች ዘንድ አሁንም ድረስ ይታወሳል፡፡ በዚያ ውድድር አልማዝ አያና ከሦስት ሺ ሜርት\nበኋላ አፈትልካ በመውጣት ውድድሩን በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ በሁለተኛነት የማጠናቀቅ ሰፊ እድል የነበራት ገንዘቤ ዲባባ ነበረች፡፡ ይሁን እንጂ ገንዘቤ ውድድሩን ለመጨረስ ከሃምሳ ሜትር ያነሰ ርቀት በቀራት ወቅት ሰንበሬ ተፈሪ ከኋላ መጥታ የብር ሜዳሊያውን ማጥለቋ ይታወሳል፡፡ ሰንበሬ በዩጂኑ ውድድር እነዚሁን የአገሯን ልጆች ጨምሮ ሌሎች ኮከቦች በሚፎካከሩበት ዳይመንድ ሊግ ተካታለች፡፡ ለተሰንበት ግደይና ፋንቱ ወርቁ በዚህ ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ናቸው፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 23/2011 ", "passage_id": "186529f7b60d89b46b4ce0fea00acab4" } ]
bc9cfed9e1edc3d24d87d74c2d9c5712
b8381aa3bb617ed9451aee1bd182f430
ጁንታው የህግ ታራሚዎችን በመቀሌ ከተማ ውስጥ በመልቀቅ ዝርፊያ እንዲፈጸም ማድረጉን የከተማዋ ከንቲባ አስተወቁ
መሀመድ ሁሴን አዲስ አበባ፡- የህወሓት ጁንታ በትግራይ ክልል ባሉ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ የነበሩ የህግ ታራሚዎችን ሰብስቦ በመቀሌ ከተማ ውስጥ በመልቀቅ ዝርፊያ እንዲፈጸም ማድረጉን የከተማዋ ከንቲባ አስታወቁ።የመቀሌ ከተማ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አታክልቲ ኃይለስላሴ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በመንግሥት የተወሰደውን የህግ ማስከበር ዕርምጃ ተከትሎ የጁንታው አባላት በክልሉ የተለያዩ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ በተለያዩ ወንጀሎች ተይዘው የእስር ጊዜያቸውን እየፈጸሙ የነበሩ ታራሚዎችን መቀሌ ከተማ ለቀዋቸዋል። በዚህም በከተማዋ ውስጥ የዝርፊያ ወንጀል እንዲፈጽሙና ህዝቡ በስጋት ውስጥ እንዲወድቅ አድርገዋል።“በበርካታ ወንጀሎች ተይዘው የነበሩ ሰዎች መቀሌ ላይ ተሰብስበው እንዲለቀቁ ስለተደረገ የግለሰቦች ሱቅ ጭምር እንዲዘረፉ ተደርጓል” ያሉት ከንቲባው፤ ይሄን ያደረጉትም አንድም ተቋማትን በመዝረፍ ሰነዶችን ለማጥፋት፣ ሁለተኛም ሕዝቡ ወደ ስጋት እንዲገባና እንዲጠራጠር በማድረግ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በአዲሱ አስተዳደር ላይ እምነት እንዲያጣ ለማድረግ መሆኑንም አስረድተዋል። በዚህ ረገድ መከላከያ ሠራዊት ወደ መቀሌ ከተማ ሲገባ ህዝቡ በደስታ የተቀበለው መሆኑን የሚናገሩት አቶ አታክልቲ፤ ጁንታው በከተማዋ በለቀቃቸው ሰዎች አማካኝነት የሚፈጠሩ የዝርፊያና ስርቆት ተግባራት መበራከት ግን ህዝቡ የደህንነት ስጋት እንዲያድርበት የሚያደርጉ ችግሮችን ፈጥረው እንደነበር ያስታውሳሉ። እነዚህ ችግሮች ደግሞ ሆን ተብለው በጁንታው የተቀነባበሩ መሆናቸውንም ነው ከንቲባው የተናገሩት። “ዝርፊያዎቹን በባህሪያቸው በሁለት ተለይተው መታየት የሚችሉ፤ ብዙ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ሆን ብሎ እንዲዘረፉ የተደረገበትም ነው” ያሉት ከንቲባው፤ ይህ የተደረገውም በተቋማቱ ውስጥ የሚገኙ ሰነዶችን ለማጥፋት አሊያም ለመውሰድ ታስቦ የተቀነባበረም ሆነ ዝርፊያ የተፈጸመበት እንደሆነም አብራርተዋል።በከተማዋ የታየው ዝርፊያ በጁንታው ትዕዛዝ የተፈጸሙ መሆናቸውን በመግለጽም፤ በተለይ በዋና ዋና መስሪያ ቤቶች ላይ ራሳቸው እዚያ ይሠሩ የነበሩ ሰዎች አንዳንድ ሰነዶችን ያጠፉበት መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህ ረገድ የከተማ አስተዳደሩ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ሙሉ ለሙሉ መዘረፉን ተናግረዋል። በተጨማሪም የሕዝብ አገልግሎት መስጫዎች የሆኑት የፍትህ ተቋማት፣ ማዘጋጃ ቤት፣ ፍርድ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ሰነዶች ተዘርፈዋል ያሉት አቶ አታክልቲ፤ በእነዚህ ተቋማት ውስጥ ሆን ተብሎ የተቀናጀ ዝርፊያ ከተፈጸመ በኋላ ተሰርቆ ነው ለማለት ተቋማቱን ክፍት አድርገው መተዋቸውንም አስረድተዋል። ይህንን አጋጣሚ የተጠቀሙ ሌሎች ዘራፊዎችም የተለያዩ ቁሳቁሶችን መዝረፋቸውንም ጠቁመዋል።አሁን ከተማው ወደ ነበረበት የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴዎች እየተመለሰ መሆኑን የሚያሳዩ ጥሩ እንቅስቃሴዎች አሉ ያሉት አቶ አታክልቲ፤ ህብረተሰቡን ያማከለ ሥራ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመሆን እየተሠራ ስለሆነ በአጭር ቀናት ውስጥ መቀሌ ወደነበረችበት መደበኛ እንቅስቃሴ እንደምትመለስ አረጋግጠዋል።ለዚህም “በከተማ ደረጃ በምናቋቁመው ምክር ቤት ሕዝቡ በቀጥታ የሚመርጣቸው የየትኛውም ፖለቲካ ፓርቲዎች አባል የሆኑና ለውጡን ደግፈው ሕዝቡን ወደ ተሻለ ደረጃ ሊያሸጋግሩ የሚችሉ አካላት ወደኃለፊነት ይመጣሉ” ያሉት ከንቲባው፤ አሁን የተፈጠረውን ጊዜያዊ ምስቅልቅል በመቆጣጠርና በመምራት ኃለፊነት ወስደው የሚሠሩ፣ ሕዝቡም የተቀበላቸው እና ጥሩ ስነምግባር ኖሯቸው በሕብረተሰቡ አካባቢ ያለውንና የሚነሱትን የፍትህ፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በፍቃደኝነት መሥራት የሚችሉ ሰዎች በሙሉ የሚካተቱበት ዕድል እነዳለ አስታውቀዋል፡ አዲስ ዘመን ታህሳስ8/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37507
[ { "passage": " ምህረት\nሞገስ አዲስ\nአበባ፡- የጁንታው\nአመራሮች እና ስትራቴጂስቶች\nመያዝ ለትግራይ ህዝብ\nትልቅ የነፃነት ተስፋ\nያነገሰ መሆኑን የትግራይ\nክልል ብልፅግና ፓርቲ\nፅህፈት ቤት ኃላፊ\nአቶ ነብዩ ስሁል\nአስታወቁ፡፡ የትግራይ ህዝብ\nለዓመታት ስርዓቱ የሚገረሰስ\nበማይመስል ደረጃ\nትልቅ ፕሮፖጋንዳ እየተነዛበትና\nአፈና እየተጫነበት መኖሩን\nአመለከቱ፡፡የጁንታው ቁንጮ አመራርና የጥፋት ስትራቴጂስቱ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ወልዱ እና ዶክተር አብረሀም ተከስተን ጨምሮ ዋነኛ የጁንታው አመራሮች መያዛቸውን ተከትሎ፤ አቶ ነብዩ ስሁል ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል እንዳስታወቁት፤ አሁን ላይ የትግራይ ህዝብ ስሜት ደስታና ተስፋ የነገሰበት ነው፡፡ በእርግጥ ከነበረው ፕሮፖጋንዳ አንፃር ነገሮችን ለማመን የተቸገረ ሰው ብዛት ቀላል ባይሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ በተለይም የጁንታው አመራሮች መያዝ ለውጡን በሙሉ ልብ ወደ መቀበሉ እየሄደ እንዳለ የሚያመላክቱ ማሳያዎች እየበዙ መጥተዋል ብለዋል።የህውሓት አጥፊ ቡድን መሪዎች መያዝ መጀመራቸው ብዙ መልዕክት እንዳለው ያመለከቱት አቶ ነብዩ፤ በዋነኛነት ከህግ አንፃር ሊጠቀስ የሚችለው ማንኛውም እና በየትኛውም ደረጃ ላይ ያለ ሰው ህግ ቢጥስ እና ቢያጠፋ በህግ ፊት የሚቀርብ እና ጊዜ ጠብቆ ተጠያቂነቱ የማይቀር መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ለትግራይ ህዝብ በተለይ ለወጣቱ የለውጥ ምዕራፍ ወለል ብሎ መከፈት መጀመሩን ያበሰረ መሆኑን አመልክተዋል፡፡‹‹ስልጣን ማለት ህዝብን ማገልገያ እንጂ የግል ጥቅም ማስጠበቂያ ርስት አይደለም›› ያሉት አቶ ነብዩ፤ ስልጣንን ከዴሞክራሲያዊነት ውጪ በአምባገነንነት መጠቀም የሚያስከትለው ውርደት መሆኑ ግልፅ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ የህውሓት ሥርዓት ቤተሰባዊ እና አፓርታይዳዊ ነበር፡፡ ስርዓቱ በአገር ደረጃ ከፋፋይ እና አፍራሽ ፖሊሲ በመከተል የግጭት እና የቅሬታ ንግድ ላይ የተመሰረተ የሥልጣን አጠባበቅ ስልት በመተግበር አገር የማፍረስ ተግባር ላይ ተሰማርቶ የቆየ እንደነበርም አስታውቀዋል። ሥርዓቱ በትግራይ ህዝብ ላይም ከፍተኛ አፈና እና በደል ሲያደርስ የቆየ እና የትግራይ ህዝብ የታገለለትን በኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር የፍትሐዊ ተጠቃሚነትና የዴሞክራሲ ዓላማዎችን ወደ ጎን በመተው ቤተሰባዊ እና ከፋፋይ ስርዓት ሲገነባ መቆየቱ መዘንጋት የለበትም ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ይህ ቡድን እስከ አሁን ላጠፋው ጥፋት በአሁኑ ጊዜ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ የሞራል እና የህግ ቅጣት እየተቀበለ የሚገኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፌዴራል መከላከያ ሠራዊት አገርን ለመበታተን አቅደው በመከላከያ ሠራዊት ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ያደረጉ አሸባሪዎችና ዋነኛ የጁንታው አመራሮች መካከል ስብሐት ነጋ እና አባይ ወልዱን ጨምሮ ከመከላከያ ከድተው ጁንታውን የተቀላቀሉ ኮሎኔሎች እና ጄነራሎችን እየያዘ ለፌዴራል ፖሊስ በማስረከብ ላይ እንደሚገኝ ይታወሳል፡፡", "passage_id": "01437f9ebaad7f4b709b183778f553bd" }, { "passage": "የትግራይ ክልል መንግስት አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ ለ957 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ።የህግ ታራሚዎቹ በሰሩት ወንጀል ተጸፅተው በይቅርታው አዋጅ መሰረት ይቅርታ የተደረገላቸው ናቸው።ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች በነገው እለት ወደ ቤተሰቦቻቸው እንደሚቀላቀሉ፥ የክልሉ ማረሚያ ቤት ፅህፈት ቤት ሃላፊ ተወካይ ኮማንደር ወልዳይ አብርሃ ተናግረዋል።ታራሚዎቹ ወደ ህዝቡ ሲቀላቀሉም የበደሉትን ማህበረሰብ በልማት ስራዎች በመሳተፍ መካስ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።ይቅርታው በሙስና፣ በህገ ወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውር የተፈረደባቸውን ታራሚዎች አይመለከትም ተብሏል።የክልሉ መንግስት ባለፈው ሰኔ ወር አጋማሽ የሰማዕታት ቀንን ምክንያት በማድረግ ለ1 ሺህ 421 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉም የሚታወስ ነው(ኤፍ ቢ ሲ)።", "passage_id": "682002e865abcb6f448fd89622be93bf" }, { "passage": "በፍኖተ-ሰላም ከተማ ውስጥ የሚገኘው ማረሚያ ቤት ዛሬ ጠዋት 2 ሰዓት ላይ በወንዶች ማረሚያ ቤት ቆጠራ ሊካሄድ ሲል በታራሚዎች መካከል አምቧጓሮ መነሳቱን የሚናገሩት የማረሚያ ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ረዳት ሳጅን ግርማ ሙሉጌታ ምክንያታቸው የአቃቢ ህጉ በቴሌቪዥን ቀርበው የሰጡት መግለጫ እንደሆነ ይናገራሉ።\n\n• በደብረ ማርቆስ ማረሚያ ቤት እሳት ተነሳ\n\n• በኬንያ በርካታ ትምህርት ቤቶች በተማሪዎች ተቃጠሉ \n\nታራሚው ለምን አንፈታም በሚል ተቃውሞ ማሰማቱን የሚናገሩት ረዳት ሳጅን ግርማ አንቆጠርም በማለት ማስቸገራቸውን ገልፀዋል። የፖሊስ አባላት የታራሚውን ማመፅ ሲያዩ ወጥተው ጥበቃ ማጠናከራቸውን ወዲያውም በማረሚያ ቤቱ የሚገኘው የሸማ ማምረቻ ክፍል በእሳት እንደተያያዘ ያስረዳሉ። \n\nጨምረውም 26 የታራሚዎች ማደሪያ ክፍሎች ሙሉ በሙሉ በእሳት መውደማቸውን፤ በእሳቱ የታራሚዎች አያያዝና የሬጅስትራር ቢሮም መቃጠሉንም ተናግረዋል። \n\nበቢሮው ውስጥ የነበሩት ኮምፒውተሮችን ማውጣት በመቻላቻው ከውድመት እንደተረፉ ገልፀዋል።\n\nበተመሳሳይ ዜና በወልዲያ ማረሚያ ቤት ዛሬ ጠዋት 2 ሰዓት ላይ እሳት መነሳቱንና ሙሉ በሙሉ የወንዶች ማደሪያ እንዲሁም የስልጠና ማዕከሉ መሳሪያዎችና ማዕከሉ መውደሙን የማረሚያ ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ኮማንደር እንዳለ ለቢቢሲ ተናግረዋል። \n\nተቃውሞው የጀመረው ሰሞኑን ስኳር ባለመኖሩ ሻይ ስላልነበራቸው ሻይ ይግባልን በማለት እንደሆነ ያስረዱት ኮማንደሩ አስከትለውም ታራሚዎቹ ድንጋይ ውርወራ መጀመራቸውን ገልፀዋል።\n\n• በደብረማርቆስ 'ባለስልጣኑ አርፈውበታል' የተባለው ሆቴል ጥቃት ደረሰበት \n\n• ቀኝ እጇን ለገበሬዎች የሰጠችው ኢትዮጵያዊቷ ሳይንቲስት\n\nእስካሁን ድረስ ሁለት ታራሚዎች መቁሰላቸውንም ጨምረው ነግረውናል።\n\nበትናንትናው ዕለት በደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት ቃጠሎ መድረሱም የሚታወስ ሲሆን አዲስ አበባ ቃሊቲና አርባ ምንጭ ውስጥ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ ታራሚዎች ተመሳሳይ የእንፈታ ጥያቄ በማቅረብ አለመረጋጋት እንደነበር ተገልጿል።\n\n ", "passage_id": "276951f7bd20f842873211d9a76dfa41" }, { "passage": "ድንገት በታራሚዎች ላይ ፍተሻ በተጀመረበት ግዜ በተፈጠረው አለመግባባት ሊያመልጡ ባሰቡ ታራሚዎች በተወሰደ ዕርምጃ ነው ጉዳቱ የደረሰው ብልዋል የማረምያ ቤቱ አስተዳደር። ", "passage_id": "eba996a8e1875cee9fe41dfc66e802bb" }, { "passage": "ከተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ጎን በመቆም የከተማቸውን ሰላም ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሽሬ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። የህወሓት የጥፋት ቡድን በህዝቡ ላይ በተለያዩ መንገዶች ሲያደርሰው የነበረው ብዙዎቹ ግፍና ጫና በአማርሮ እንደነበር  ነዋሪዎቹ ይናገራሉ። “ህልውናችሁ የህወሓት ቡድን ብቻ ነው፣ ህወሓት ከሌለ ትግራይና ህዝቧ አይኖርም” በማለት ጁንታው ሲያደናግር እንደነበር  ኢዜአ ያነጋገራቸው የሽሬ ከተማ ተናግረዋል። የህወሓት ታጣቂ ቡድን ይባስ ብሎ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ምሽት ላይ የትግራይ ህዝብ መከታ እና የልማት አጋር የነበረውን የሰሜን ዕዝ በማጥቃት የጭካኔውን ጥግ ማሳየቱንም ነው ነዋሪዎቹ የጠቀሱት። ድርጊቱ በሃይማኖትም የተወገዘ ከሰብዓዊነትም የወጣ እኩይ ተግባር መሆኑን የሽሬ ከተማ ነዋሪው መልዕከ ሰላም ገብረዋህድ ገብረማርያም ገልጸውልናል። “የሰውን ልጅ ያውም ወገንን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል ለአሞራና ጅብ የሰጠ የህወሓት ቡድን የትግራይ ህዝብ ወኪል ነኝ ቢል ማንም የሚሰማው የለም” ብለዋል። የትግራይ ህዝብ ከአገር መከላከያ ሰራዊት ጋር እጅ እና ጓንት ሆኖ አብሮ እየበላ፣ ተዛምዶና ተዋልዶ የኖረ ስለመሆኑም አንስተዋል። ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ ሃጂ ሙሃመድ ሙርሃን ሲራጅ፤ “የመከላከያ ሠራዊት የህዝብ ልጅ እንጂ ወራሪም ጠላትም አለመሆኑን የትግራይ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቃል” ብለዋል። ሠራዊቱ የአርሶ አደር አዝመራ ሲሰበስብ፣ አንበጣ ሲያባርር እና በብዙ አጋጣሚዎች አብሮነቱን በተግባር ያሳየ የትግራይ ህዝብ ቤተሰብ መሆኑንም ጠቅሰዋል። “ይህንን የህዝብ አጋር የሆነ ሠራዊት ላይ ጥቃት የፈጸመው የህወሓት የጥፋት ቡድን የትግራይ ህዝብ ጠላት መሆኑን በግልጽ አሳይቷል፤ በቁጥጥር ሥር ውሎ በህግ ተጠያቂ መሆን ይኖርበታልም” ብለዋል ሃጂ ሙሃመድ። በጥፋት ተግባር የተሰማራው የህወሓት ቡድን በፈፀመው ወንጀል በህግ ተጠያቂ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ህዝቡ በየአካባቢው ሰላሙን በማረጋገጥ ልማቱን እንዲያስቀጥል ጊዜያዊ አስተዳደር መቋቋሙ ተገቢ መሆኑንም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። ከጊዜያዊ አስተደደሩ ጋር በመሆን ለከተማው ሰላምና ልማት በጋራ እንደሚሰሩም ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል። በተለይ ወጣቶች ለከተማቸው ብሎም ለአገራቸው ሰላም የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ነዋሪዎቹ ጠይቀዋል። በሽሬ ከተማ በአሁኑ ወቅት ሰላማዊ እንቅስቃሴ መኖሩን በስፈራው የተገኘው የኢዜአ ሪፖርተር አረጋግጧል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን የተሾሙት ዶክተር ሙሉ ነጋ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ በህዝብ ምርጫ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ በማቋቋም ላይ ይገኛሉ።", "passage_id": "31e1108910ee665f2c05bf9d09e3d2fc" } ]
4fd75355e29a2876aa4ff66041cfc19a
7eb7b13444dfc85cd80d9b906176bc4c
በኮሮና ዙሪያ የሚስተዋለውን መዘናጋት ለመቅረፍ የማንቂያ መርሃ ግብር ተጀመረ
በኃይሉ አበራአዲስ አበባ፡- በሀገራችን በኮቪድ-19 ዙሪያ በህብረ ተሰቡ መካከል ሰፊ መዘናጋቶች እየታየ በመሆኑ በርካቶች በቫይረሱ እየተያዙ እና ለሞት እየተዳረጉ በመሆኑ መዘናጋቱን ለመቅርፍ የሚያስችል ለአንድ ወር የሚቆይ የማንቂያ መርሃግብር መጀመሩን የአራዳ ክፍለ ከተማ የወጣቶች አደረጃጀት አባላት ገለጹ። የአራዳ ክፍለ ከተማ የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች አምባሳደር ረሂማ ዋበላ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጠችው አስተያየት በክፍለ ከተማው 20 የሚሆኑ የተለያዩ የወጣት አደረጃጀት በጎ ፈቃደኛ አምባሳደሮች ኮቪድ-19 መከላከልን ጨምሮ በትምህርት ቤቶች፣ በአረጋውያን ቤት እድሳት እና በመሳሰሉት የበጎ ፍቃድ ስራዎች እየሰሩ ይገኛሉ። በተለይ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላል በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ መዘናጋት እየተስተዋለ በመሆኑ ህብረተሰቡ ካለበት ሰፊ መዘናጋት እንዲነቃ እና ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲወስድ ለማንቃት ሰፊ ስራ እየተሰራ ይገኛል ብላለች።የንቅናቄው ዓላማ ህብረተሰቡ ግንዛቤ ቢኖረውም እንኳ ባለው መዘናጋት የተነሳ ለኮቪድ-19 እየተጋለጠ በመሆኑ እያንዳንዱ ሰው በሁሉም አካባቢ ርቀቱን እንዲጠብቅ፣ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ማስኮችን በአግባቡ እንዲጠቀም፣ እጅን በውሃና በሳሙና ደጋግሞ እንዲታጠብ እና አልኮል ወይም ሳኒታይዘር እንዲጠቀም የማስታወስ ስራ እየሰሩ መሆናቸውን ወጣት ረሂማ ተናግራለች። የአራዳ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ አቶ ተካ ደመቀ በበኩሉ እንደገለጸው በኮቪድ-19 ዙሪያ አስፈላጊ ጥንቃቄ ማድረግን እየዘነጋ የመጣውን ማህበረሰባችንን ለማንቃት በሚል በትናንትናው እለት በተጀመረው የማንቂያ መርሃ ግብር ለቀጣይ አንድ ወር የሚቆይ ሰፊ ንቅናቄ ይሰራል።በአንድ ወር ቆይታውም በጎ ፈቃደኛ ወጣት አምባሳደሮችንና ሌሎች ወጣት አደረጃጀቶችን በየቦታው በማስተባበር፣ ህብረተሰቡ ርቀቱን እንዲጠብቅ፣ ማስክ በአግባቡ እንዲያደርግ ከመዘናጋቱ እንዲነቃ እና ሌሎችንም እንዲያስተምር ተደጋጋሚ ንቅናቄ ይደረጋል ብሏል።ከዚህ በፊት በአራዳ ክፍለ ከተማ ደረጃ ሰፊ የማንቂያ ንቅናቄ ሲሰራ መቆየቱን ያስታወሰው አቶ ተካ በዚህ ሁለተኛ ዙር የማንቂያ መርሃ ግብር ህብረተሰቡ መዘናጋቱን በመስበር እና ከራሱ ጀምሮ ኃላፊነቱን በመወጣት ኮሮናን በመከላከሉ ረገድ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አሳስቧል። በማንቂያ መርሃ ግብሩ ላይ የክፍለ ከተማው የበጎ ፍቃደኛ አምባሳደሮችን ጨምሮ የተለያዩ ወጣት አደረጃጀቶች ከአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በመነሳት በአራት ኪሎና በስድስት ኪሎ በኩል በመጓዝ ሰዎች በሚበዙበት አካባቢዎች የማንቃት ስራዎችን ሰርተዋል።በዓለም ዙሪያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ወዲህ ከ73 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውንና ከአንድ ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ደግሞ በዚሁ የተነሳ ለሞት መዳረጋቸውን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃዎች ያሳያሉ።አዲስ ዘመን ታህሳስ 7/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37472
[ { "passage": "ወይዘሮ የማታ ግርማና ወይዘሮ መንበረ ተድላ ጎረቤታሞች ናቸው፡፡ ጎረቤታሞቹ ኮቪድ 19 ወረርሽኝ በሽታን ለመከላከል የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ የአንበሳ አውቶቡስ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመጠቀም በመስኮት ለትኬት ቆራጯ ሳንቲም ለመስጠት ይንጠራራሉ፡፡ ትኬት ቆራጯ አፋቸውን ካልሸፈኑ መጠቀም እንደማይችሉ ነገረቻቸው፡፡ ትዕዛዟን ከመቀበል ይልቅ ተከራከሯት፡፡ አገልግሎቱን እንደማያገኙ ሲያውቁ ሁለቱም በትራንስፖርቱ አቅራቢያ የአፍ መሸፈኛውን ገዝተው በመጠቀም አገልግሎቱን ያገኛሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ነበር ስለበሽታው ያላቸውን ግንዛቤ እንዲነግሩኝ የጠየኳቸው፡፡\nሁለቱም እጅን መታጠብ፣ አፍና አፍንጫን መሸፈን፣ ርቀትን መጠበቅ በሽታውን ለመከላከል አስፈላጊ እንደሆነ ግንዛቤው አላቸው፡፡ ከአንበሳ ትኬት ቆራጯ ጋር ስለነበረው አለመግባባት እንደነገሩኝ እነርሱ በነጠላቸው አፋቸውን መሸፈን እንደሚችሉ ሲነግሯት፣ እርሷ ደግሞ የአፍና አፍጫ መሸፈኛ(ማስክ) መጠቀም ግዴታ ነው የሚል ነበር ምላሿ፡፡ በሌላ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ በነጠላቸው መጠቀም በመቻላቸው እንደተከራከሯት ነው የተናገሩት፡፡\nእንደነ ወይዘሮ የማታ አስተያየት ጥንቃቄው ወጥነት የለውም:: አንዳንድ የሕዝብ ትራንስፖርት መስጫዎች በነጠላ መሸፈንን ይከለክላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ይፈቅዳሉ፡፡ ለተሳፋሪው የእጅ ንጽህና መጠበቂያ አልኮልና ሳኒታይዘር ማቅረብም እንደጅምሩ ሆኖ አላገኙትም፡፡ በጣም ጥቂት የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ናቸው የሚያቀርቡት፡፡ በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ባለበት በዚህ ወቅት ጥንቃቄው የላላው በአገልግሎት ሰጪዎችም በኩል እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡\nወይዘሮ የማታ እና መንበረ በመገናኛ ብዙኃን ሲተላለፍ ከሚሰሙት መረጃ ውጪ በበሽታው የተጎዳ በአካባቢያቸውም ሆነ በቤተሰብ እንዳላጋጠማቸው በማስታወስ፣ ይሄ እነርሱን ጨምሮ ብዙዎችን አዘናግቷል ብለው ያምናሉ፡፡ ወደ ገበያም ሆነ ለተለያየ ጉዳይ ሲወጡ ብዙዎች የአፍ መሸፈኛ ቢያደርጉም በአግባቡ ሲጠቀሙበት አለማስተዋላቸውን ተናግረዋል፡፡ በግላቸው አስገዳጅ ካልሆነ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛውን ባይጠቀሙ ይመርጣሉ፡፡ በአጠቃቀሙ ላይ በተለያዩ አካላት የሚሰጠው አስተያየትም መሸፈኛውን ለመጠቀም የሚያበረታታ እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡ \nኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሽታ መኖሩን በመገናኛ ብዙኃን ስትሰማና ከቤት ስትወጣ አፍና አፍንጫቸውን የሸፈኑ ሰዎችን ስታይ እንደሆነ አስተያየቷን የሰጠችን ወጣት ኤደን በቀለ በቤት ውስጥ የሚውሉ ሴቶች ተሰባስበው ቡና ሲጠጡ ወጣት ወንዶችም እንዲሁ ተሰብስበው ካርታ ሲጫወቱ፣ አዋቂ ወንዶችም ከመጠጥ ቤት እንደማይጠፉ መታዘቧን ተናግራለች፡፡\nብዙዎችም ስለበሽታው ከሚያደርጉት ጥንቃቄ ይልቅ በበሽታው የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ለማወቅ ያላቸውን ጉጉት ታዝባለች፡፡ ትዝብቷ እንድትዘናጋ እንዳደረጋትም ተናግራለች፡፡ከቤት ስትወጣ ግን የአፍ መሸፈኛ እንደምትጠቀም ገልጻለች፡፡\nበጋራ መኖሪያቤት ውስጥ እንደሚኖሩ የነገሩኝ ወይዘሮ አመለወርቅ ታደሰ ወረርሽኙ እንደተከሰተ አካባቢ በሕንፃቸው ላይ ለእጅ መታጠቢያ ውሃና ሳሙና እንዲሁም ሳኒታይዘር በማዘጋጀት ብዙዎች ጥንቃቄ ሲያደርጉ እንደነበር በማስታወስ፣ አሁን ግን እንደጅምሩ አይደለም ይላሉ፡፡ በግላቸው የእጅ መታጠቡ ልማድ ሆኖባቸው ጥንቃቄ ማድረጉን እንዳጠናከሩ ይገልጻሉ፡፡ ልጆቻቸው ላይ ግን መዘናጋት ማስተዋላቸውንና ቢመክሯቸውም እንዳልተቀበሏቸው ገልጸዋል፡፡ የብዙዎች መዘናጋትም አስፈርቷቸዋል፡፡\nበገበያ ቦታ ያገኘናቸው ወይዘሮ ቀፀላ ይትባረክ ከበሽታው እራሳቸውንና ሦስት ቤተሰቦቻቸውን ለመከላከል የሚያደርጉትን ጥረት እንደነገሩን፣ ለቅሶ መድረስ፣ ቤተክርስቲያን መሄድ ትተዋል:: በሽታው ከተከሰተ ከቤታቸው ርቀው መሄድ ቀንሰዋል:: ወጥተው ሲመለሱም ልብስ ይቀይራሉ፡፡ ይታጠባሉ፡፡ ቤተሰቦቻቸውም በተመሳሳይ እንዲያደርጉ ይከታተሏቸዋል፡፡በሽታው እስኪጠፋ ድረስ የግል ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ መክረዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ በመንደሮች፣ በንግድ ቦታዎች፣ በመንገድ ላይ በትራንስፖርት አገልግሎት መስጫዎች ተዘዋውረን እንዳየነው ቅድመ ጥንቃቄው ገና ይቀረዋል፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 6/2012ለምለም መንግሥቱ", "passage_id": "f6aa737fbc18fef4aa97f32402fb2644" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ሁለተኛ ዙር በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ የቤት ለቤት የኮቪድ-19 አሰሳ ተጀምሯል።የሁለተኛው በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ የቤት ለቤት የኮቪድ-19 አሰሳ በዋናነት ህብረተሰቡን ማስተማር እና የተገኙ መረጃዎችና ውጤቶች በፍጥነት በማስተላለፍ በሽታውን ለመከላከል የሚደረጉ ጥረቶችን ለማገዝ ከፍተኛ ሚና ሊጫወት እንደሚችል የጤና ሚንስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ተናግረዋል፡፡በኢትዮጵያ የበሽታው ቁጥር መጨመር በጀመረበት በአሁኑ ወቅት የሚስተዋል መዘናጋትና ቸልተኝነት ሊታረም እንደሚገባም ጨምረው መግለፃቸውን የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።በአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ዶክተር ሙሉጌታ እንዳለ በበኩላቸው፥ ሁለተኛው በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ የቤት ለቤት የኮቪድ-19 አሰሳ በመጀመሪያው መረሀግብር የተስተዋሉ ክፍተቶችን በመሸፈን አስፈላጊን ውጤት ማስመስገብ የሚያስችል ነው ብለዋል።በመጀመሪያው የቤት ለቤት አሰሳ መረሀግብር 3 ነጥብ 1 ሚሊየን የሚሆኑትን የህብረተሰብ ክፍል ማዳረስ የተቸለ መሆኑን ዶክተር ሙሉጌታ ገልጸዋል።በዚህም 971 ተጠርጣሪዎች የተለዩ ሲሆን፥ ከንአዚህም ውስጥ 21 ሰዎች ምልክት የታየባቸው እና 1 ሰው ደግሞ ቫይረሱ እንደተገኘበት ተነግሯል።በመጀመሪያው ዙር በዜጎች ዘንድ ይቃደኛ ያለመሆን፣ ቤት ዘግቶ የመጥፋት እና መልክቶችን መጨመርን ጨምሮ ሌሎች ያለመተባበር ችግሮች እንደተስተዋሉ ተመልክቷል።ህብረተሰቡም ለተጀመረው 5ኛው ዙር በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ የቤት ለቤት አሰሳ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ማድረግ እንዳለበትም ጥሪ አስተላልፈዋል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "89260609fa1e82e25864b2fc3370132a" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አምስቱን የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ማክበሩን ዛሬም ቀጥሏል ፡፡በዚህም ዛሬ የብሩህ ተስፋ ቀን በሚል መሪ ቃል ቀኑ እየተከበረ ሲሆን ÷ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች የቢጫ ታክሲ አሽከርካሪዎች ትርዒት ሲያሳዩ አርፍደዋል፡፡ከትርዒቱ ጎን ለጎንም ቀኑን ሚገልፁ መልዕክቶች ተላልፈዋል፡፡መርሃ ግብሩ ቀጥሎ የሚውል ሲሆን የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በቅርቡ ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ የጠቃጠሉ 30 የሚሆኑ ቤቶች እና ሱቆችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡በቅርቡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሲ.ኤም.ሲ አሊታድ ሚካኤል የደረሰው የእሳት አደጋ 12 ሚሊየን ብር የሚገመት 18 የንግድ ሱቆች ፣11 መጋዘኖች እና አንድ ባርና ሬስቶራንት ላይ ጉዳት ማድረሱ ይታወሳል፡፡በፍሬህይወት ሰፊው\nየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "d985f32a1b270b8da912627b2d6fce3b" }, { "passage": "አዲስ አበባ:- ጊፍት ሪል እስቴት በመንግሥት እየተደረገ የሚገኘውን የጸረ ኮቪድ- 19 እንቅስቃሴን በማጠናከር የቫይረሱን ስርጭት በአገሪቱ ለመግታት ለሚደረገው እርብርብ የሚውል የአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ። የንግዱ ማህበረሰብ የተፈጠረውን የጤና ቀውስ ተጠቅሞ ያልተገባ ትርፍ ለማግበስበስ ከላይ ከታች የሚልበት ሳይሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ ከህዝብና ከመንግሥት ጎን ሊቆም የሚገባበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል። \nድርጅቱ የጸረ ኮቪድ 19 ወረርሽኝን እንቅስቃሴን አስመልክቶ ትናንት በሰጠው መግለጫ የጊፍት ቢዝነስ ግሩፕና የጊፍት ሪል እስቴት መስራችና ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ገብረየሱስ ኢጋታ እንደገለጹት፤ ኮቪድ- 19 የተባለው ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ በአገሪቱ መግባቱ በምርመራ ከተረጋገጠበት ጀምሮ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት በሚደረገው እርብርብ ድርጅቱ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በተጨማሪም ድርጅቱ በመንግሥት እየተደረገ የሚገኘውን የጸረ ኮቪድ- 19 እንቅስቃሴን በማጠናከር የቫይረሱን ስርጭት በአገሪቱ ለመግታት ለሚደረገው እርብርብ የሚውል የአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። \nኮቪድ 19 ያደገ ኢኮኖሚና ደረጃውን የጠበቀ የጤና መሰረተ ልማት ባላቸው አገራት ጭምር ቫይረሱን ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ ባቸው እንደ ሰደድ እሳት እየለበለባቸውና እንደ አውሎ ንፋስ ዓለምን እያደረሰ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ቫይረሱ መገኘቱ ይፋ ከተደረገ ወዲህ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ከዕለት ወደ ዕለት እያሻቀበ እንደሚገኝ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፤ ድርጅቱ የኮቪድ 19 ቫይረስ ስርጭትን በአገሪቱ ለመግታት ከመንግሥት የተላለፈውን ጥሪ መሰረት በማድረግና የሚጠበቅበትን ማህበራዊ ኃላፊነት ከመወጣት አንጻር የተለያዩ ተግባራትን እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። \nእርሳቸውም ለአብነት የበሽታውን አምጭ ቫይረስ ለመከላከል በዋነኝነት የግል ንጽህናን መጠበቅ ግንባር ቀደሙ የመከላከያ መንገድ በመሆኑ፤ ድርጅቱ በመዲናዋ በርካታ ሰው በሚንቀሳቀስባቸውና የእጅ መታጠቢያ\n ውሃ እጥረት ባለባቸው ሰባት አካባቢዎች ላይ ባለ አንድ ሺ ሊትር ውሃ የሚይዝ በርሜል፣ ሳሙናና ሌሎች የጸረ ጀርም ግብዓቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ህብረተሰቡ ንጽህናውን እንዲጠብቅ የማድረግ ሥራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። \nየድርጅቱ ሰራተኞችና በጎ ፍቃደኞችን በማስተባበር በሽታውን መከላከል በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ የተለያዩ የግንዛቤ መስጨበጫ ሥራዎችን የማከናወን ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ድርጅቱ በበጎ አድራጎት ድርጅቶች እየተረዱ ለሚኖሩ አረጋውያን በሽታውን ለመከላከል የሚረዱ ግብዓቶችን እያቀረበ የሚገኝ ሲሆን፤ ለመቄዶኒያ አረጋውያን መርጃ ማዕከል ለሚገኙ አረጋውያን የንጽህና መጠበቂያ የሚውል ጠጣርና ፈሳሽ ሳሙናዎችን፣ አንድ ሺ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ማስኮችን እንዲሁም አንድ ሺ ሊትር ውሃ የሚይዝ በርሜል ወጥነት ካለው የውሃ አቅርቦት ጋር መቅረቡን ተናግረዋል። \nከላይ የተዘረዘሩት ድጋፎች የበሽታው ስርጭት በአገሪቱ እስከሚገታ ድረስ ተጠናክሮና ተስፋፍቶ እንደሚቀጥል በድርጅቱ ስም አቶ ገብረየሱስ አረጋግጠው፤ ድርጅቱ በግል እያከናወናቸው ካሉ ተግባራት በተጨማሪ ወረርሽኙ በሚያስከትለው ኢኮኖሚያዊ ጫና ምክንያት የምግብ እጥረት ለሚያጋጥማቸው ዜጎች የምግብ አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ፤ ከሌሎች በጎ ፈቃደኛ የቢዝነስ ድርጅቶችና ግለሰቦች ጋር በመሆን ከየካ ክፍለ ከተማ የምግብ መጋዘን ተረክቦ የተለያዩ ለምግብነት የሚውሉ ግብዓቶችን የማሰባሰብ ሥራ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። \nበሌላ በኩል የንግዱ ማህበረሰብ የተፈጠረውን የጤና ቀውስ ተጠቅሞ ያልተገባ ትርፍ ለማግበስበስ ከላይ ከታች የሚልበት ሳይሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ ከህዝብና ከመንግሥት ጎን ሊቆም የሚገባበት ወቅት መሆኑን አሳስበው፤ የንግዱ ማህበረሰብ ሰርቶ ማግኘት የሚቻለው ህዝብና መንግሥት ሲኖር መሆኑን አውቆ፤ የተፈጠረውን ችግር እንደ ምክንያት በመውሰድ ለህብረተሰቡ የሚያቀርበውን ግብዓት በመደበቅ ሰው ሰራሽ የዋጋ ውድነት በመፍጠር ዋጋ ጨምሮ ሳይሸጥ ያለውን አካፍሎና ተጋግዞ ይሄን የፈተና ወቅት ማለፍ እንደሚገባ አጽኖት ሰጥተው ተናግረዋል።አዲስ ዘመን መጋቢት 23/2012\nሶሎሞን በየነ", "passage_id": "5c384539eadfa2628a2e5ed24d4b1c2a" }, { "passage": " በአሁኑ ወቅት የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የምናልፈው ከአምላክ ዕርዳታ ጎን ለጎን የእኛም ጥንቃቄ ሲታከልበት በመሆኑ ሁላችንም ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲል አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ አሳሰበ፡፡ አርቲስት ሰለሞን ከሌሎች የኪነጥበብ ባለሙያዎች ጋር በመሆን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን አስታውቋል።አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ\nለአዲስ ዘመን እንደገለፀው፤\nህብረተሰቡ ከኮሮና ቫይረስ\nራስን እንዲጠብቅ በቂ  ባይሆንም ኪነ\nጥበባዊ የግንዛቤ ማስጨበጫ\nሥራዎችን እየሠሩ ይገኛሉ\nነገር ግን በህብረተሰቡ\nዘንድ አሁንም ሙሉ\nለሙሉ የሚያስብል ተጨባጭ\nለውጥ እየታየ አይደለም\nምክንያቱ ደግሞ ህብረተሰቡ\nይህን ክፉ በሽታ\nንቆታል ወይ ደግሞ\nተዘናግቷል ማለት ነው\nስለዚህ ገና ብዙ\nመሠራት አለበት፡፡ በዚህ\nጉዳይ ግንዛቤ ያለው\nሁሉ ህብረተሰቡን ማስተማር\nአለበት፡፡እኛ እንደባለሙያተኛና እንደግል\nመደረግ ያለባቸውን ጥንቃቄዎች\nበሙሉ ለህብረተሰቡ በማስገዘብ\nላይ እንገኛለን ያለው\nአርቲስት ሰለሞን፤ ሰሞኑን\nከትራፊክ  ፖሊሶችና\nከቀይ መስቀል ጋር\nበመሆን አውቶብስ ተራ፣\nመርካቶ፣ ተክለ ሃይማኖት\nአካባቢዎች እንዲሁም ቄራና\nአካባቢው መልዕክት ማስተላለፋቸውን\nጠቁሟልአሁን ደግሞ ሕብረት ለበጎ በሚል በተቋቋመው ፋውደሽን በኩል የጽዳትና የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጨርቆችን በመግዛት ለሊስትሮና ለጎዳና ተዳዳሪዎች እንደሚያከፋፍሉ ተናግሯል። አብዛኛው ህዝብ የዕለት ጉርሱን በየቀኑ ፈላጊ በመሆኑ ዝም ብሎ ቤቱ ሲቀመጥ ለከፋ ችግር ይዳረጋል  ያለው አርቲስ ሰለሞን፣ ህብረተሰቡ ከኮሮና ቫይረስ ራሱን መከላከል እንዲችል እያዝናና ከማስተማር ጎን ለጎን ያላቸው ለሌላቸው ድጋፍ እንዲያደርጉም ጭምር መልዕክት አስተላልፏል“እኛም አርቲስቶች የህክምና ባለሙያዎችንና የመንግሥት ውሳኔዎችን ባከበረ መንገድ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶችን በማቅረብ ድጋፍ ማድረግ ይኖርብናል” ብሏል።በዚህ ቀውጢ ጊዜ መረዳዳት እንጂ መጎዳዳት አያስፈልግም ያለው አርቲስት ሰለሞን ጊዜው ትርፍ የምናጋብስበት ሳይሆን ተደጋግፈንና ተዛዝነን ልናልፈው የሚገባ ወቅት ነው ሲልም አስተያየቱን አካፍሎናል።አዲስ ዘመን ሚያዚያ 9/2012በጋዜጣው ሪፖርተር", "passage_id": "50b2872bdf61b6ce0b89d629cfb5873c" } ]
9339865edb1be7e89a258ebcbc6c0f1a
34ba122f71fefb037606c9fcafc7d422
አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ውስጥ በሚፈለገው ደረጃ ኢንቨስት እንዳላደረጉ ተገለጸ
ፋንታነሽ ክንዴአዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ ኢንቨስት የሚያደርጉ አፍሪካውያን ባለሀብቶች ቁጥር በሚፈለገው ደረጃ አለማደጉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ከአፍሪካ አገሮች ለመጡ ባለሀብቶችና ሚሽን አባላት በተሻሻለው የኢንቨስትመንት ህግ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥቷል።የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ፣ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ የመጀመሪያው ኢንቨስትመንት ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ከአፍሪካ በተለይም ከሱዳን ነበር። በአሁኑ ወቅትም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ አፍሪካውያን ባለሀብቶች ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም። ሆኖም ተሳትፏቸው የሚፈለገው ደረጃ ላይ አልደረሰም።እንደ ኮሚሽነር ለሊሴ ገለጻ፤ አፍሪካውያን በኢትዮጵያ በከፍተኛ ደረጃ ኢንቨስት እንዲያደርጉና ጠንካራ የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲፈጠር ይፈልጋል። ከዚህ አንጻር የተመዘገቡ የኢንቨስትመንት ቁጥሮች ግን ዝቅ ብለው እንደሚገኙ ነው። ይሄን ችግር ከማቃለል አኳያም የኢንቨስትመንት ህጉ መሻሻሉን ተከትሎ ኮሚሽኑ ከኤምባሲዎች፣ ከኢንቨስትመንት ጋር ግንኙነት ካላቸው የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፣ ከልማት አጋሮች እና ከተለያዩ አገሮች ከመጡ ኢንቨስተሮች ጋር ተከታታይ ውይይቶች አካሂዷል። አዲሱን የኢንቨስትመንት ህግ ለማስረዳትም ጥረት ተደርጓል። በተደረጉ ተከታታይ ውይይቶች ባለሀብቶች ያሉባቸውን ችግሮች በተሻለ ደረጃ ለመገንዘብ ዕድል መፍጠሩን ያስታወቁት ኮሚሽነሯ፤ ይህም በቀጣይ ኮሚሽኑ ምን ዝግጅት ማድረግ እንዳለበት ለመረዳት ማስቻሉን ገልጸዋል። ተሳታፊዎችም በውይይቱ ደስተኞች እንደሆኑና በ2021 ላይ የተሻለ ውጤት እንደሚጠብቁ ገልጸውላቸዋል።ኮሚሽኑ ከትናንት በስቲያ ከአፍሪካ አገሮች ለመጡ ባለሀብቶችና ሚሽን አባላት በተሻሻለው የኢንቨስትመንት ህግ ዙሪያ ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን፤ ከማብራሪያው በኋላ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። ከተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ለመጡ ባለሀብቶችና ሚሽን አባላት ጋር የተደረገው ምክክር ህጉ ከተሻሻለ በኋላ የተካሄደ ስድስተኛ መድረክ መሆኑ ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 7/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37459
[ { "passage": "ሁሉም እርሻዎች የዕቅዳቸውን 30 በመቶ እንኳ ማሳካት ሳይችሉቀርተዋልአራት የህንድ፣ አንድ የሳዑዲና አንድ የቱርክ ሰፋፊ እርሻዎች የተካተቱበት አዲስ ጥናት ይፋ እንዳደረገው፣ ሳዑዲ ስታርን ጨምሮ ስድስት ኩባንያዎች ለአካባቢ፣ ለማኅበረሰቦችና ለድህነት ቅነሳ ተስማሚነት የጎደለው የኢንቨስትመንት እቅስቃሴ ሲያካሄዱ መቆየታቸውን ይፋ አደረገ፡፡ ሁሉም ኩባንያዎች ስለሰፋፊ እርሻ ዕውቀቱም ክህሎቱም አልነበራቸውም ተብሏል፡፡ ጥናቱን ያካሄዱትና የጥናት ውጤቶቻቸውን በመጽሐፍ አሳትመው በቅርቡ ለንባብ ያበቁት አጥቅየለሽ ጂ.ኤም. ፕርሰን (ዶ/ር) የተባሉ ኢትዮጵያዊ ምሁር በተለይ ከሪፖርተር ጋር ባደረጉት ቆይታ ይፋ እንዳደረጉት፣ በጋምቤላና በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልሎች በምግብ ሰብል ምርት ብሎም በባዮፊውል ተክሎች ልማት ለመሠማራት ፈቃድ ካወጡበት ሂደት ጀምሮ እስከ ትግበራ በነበራቸው እንቅስቃሴ ብሔራዊ ፓርክን ጨምሮ ውኃ ገብ መሬቶችን፣ ጥብቅ ደን መሬቶችንና በእርሻዎቹ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ህልውና አደጋ በሚጥል ሁኔታ የእርሻ ሥራቸውን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡ ይህም ሆኖ አንዳቸውም በአካባቢና በሰዎች ላይ ካደረሱት ጉዳት በቀር ይህ ነው የሚባል ውጤት ሳያስገኙ የአገሩን ሀብት ለኪሳራ ዳርገዋል ያሉት አጥቅየለሽ (ዶ/ር)፣ ያለ በቂ ዕውቀትና ክህሎት ወደ እርሻ ሥራው መግባታቸውም በአገሪቱ ላይ የደረሰውን ጉዳት እንዳባባሰው አብራርተዋል፡፡ ከኢንቨስትመንት አኳያ ከ70 በመቶ ካፒታል ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ተበድረው ሥራ መጀመራቸው የተነገረላቸው ኩባንያዎች፣ ከሁለት እስከ አራት ዓመታት ባለው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ የኦፕሬሽን ሥራዎቻቸውን በማሳካት ውጤት እንደሚያስመዘግቡ ቢያቅዱም፣ አንዳቸውም 30 በመቶ እንኳ ማሳካት እንዳልቻሉ አጥቅየለሽ (ዶ/ር) በመጽሐፋቸው አመላክተዋል፡፡ የሼክ መሐመድ አል አሙዲ ንብረት የሆነው ሳዑዲ ስታር፣ እንዲሁም የህንዳዊው ሳይ ራማክሪሽና ካሩቱሪ ኩባንያ የጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክን ከፊል ይዞታ ቆርሶ የሚወስድ ሰፊ መሬት ወስደዋል፡፡ ሳዑዲ ስታር ከአሥር ሺሕ ሔክታር በላይ መሬት በመውሰድ በአብዛኛው ሩዝ ለማምረት እንቅስቃሴ ቢጀምርም አልሆነለትም፡፡ ካሩቱሪ አግሮ ፕሮዳክት የተሰኘው ኩባንያም፣ በ100 ሺሕ ሔክታር መሬት ላይ የፓልም ዘይት ተክል፣ ሸንኮራ አገዳ፣ ሩዝ፣ በቆሎና ጥጥ ለማምረት በሰፊው እንደሚገባ ሲጠበቅ በእንጭጩ ቀርቷል፡፡ ሌሎቹም በተመሳሳይ ሁኔታ ከመንገድ መቅረታቸውን አጥኚዋ አብራርተዋል፡፡ ሳዑዲ ስታር በአራት ዓመታት ውስጥ መቶ በመቶ የሰብል ምርት በአራት ዓመታት ውስጥ እንደሚያሳካ ቢወጥንም፣ ከአምስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ያከናወነው የዕቅዱን 3.5 በመቶ ብቻ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ካሩቱሪ በበኩሉ ሥራ በጀመረ በሁለት ዓመታት ውስጥ ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ እንደሚተገብር ቢያስታውቅም፣ በአምስት ዓመታት ውስጥ ሊያሳካ የቻለው ግን 30 በመቶ ብቻ ሆኗል፡፡ ቶረን አግሮ ኢንዱስትሪ የተሰኘ ኩባንያም በሦስት ዓመታት 28 በመቶ የዕቅዱን ሲያከናውን፣ ኤስ ኤንዴ ፒ ኢነርጂ ሶሉሽንስ የዕቅዱን ሰባት በመቶ በአራት ዓመታት ውስጥ አከናውኗል፡፡ ሩኪ አግሪ እንዲሁም ቢኤችኦ ባዮ ፕሮዳክትስ የተሰኘው ኩባንያም በአራት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት ያቀደውን የግብርና ሥራ ትልም፣ በሦስት ዓመታት ውስጥ ከ22 በመቶ በላይ ሊገፋበት ሳይችል በኪሳራ ወጥቷል፡፡  እንዲህ ያለውን የወረደ አፈጻጸም ያስመዘገቡት የውጭ ኩባንያዎች ብቻም ሳይሆኑ፣ የመንግሥት ተቋማትም ከፍተኛ የአቅም ችግርና የክትትል ድክመት ስለነበረባቸው፣ በክልልና በፌዴራል መንግሥት መካከል በነበሩ የአሠራር ክፍተቶች፣ በመሠረተ ልማት እጥረትና በሌሎችም ችግሮች ሳቢያ የሰፋፊ እርሻዎች ውጥን ከግብ ሳይደርስ በመንገድ መቅረቱን አጥኚዋ አስረድተዋል፡፡ ኩባንያዎቹ በሚገቡበት ወቅት የእርሻ ሥራቸውን በሚያከናውኑባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ማኅበረሰቦች ስለኩባንያዎቹ መግባት እንዲያውቁና እንዲመክሩበት፣ ሐሳባቸውንም እንዲያካፍሉ አለመደረጉ ለእርሻዎቹ መውደቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም አጥቅየለሽ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ የማኅበረሰቦቹን ፍላጎትና ሐሳብ የመንግሥት ተቋማትም ሆኑ ባለሀብቶቹ ቸል በማለታቸው ሳቢያ በአካባቢ ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን፣ በተለይም እንደ ካሩቱሪ ያሉ ኩባንያዎች በዘረጉት የተሳሳተ የመስኖ እርሻ መሠረተ ልማት በእርሻው ከሚገኙ መካከል የሦስት ቀበሌ መንደሮች ሙሉ ለሙሉ በጎርፍ እንዲጥለቀለቁ መንስዔ መሆኑን አውስተዋል፡፡ መንግሥት በሰፋፊ እርሻዎች ላይ ፍላጎት ካለው እንዲህ ያሉ ችግሮችን በማጤን ለወደፊቱ እንዲያስተካክላቸው የጠየቁት አጥቅየለሽ (ዶ/ር)፣ ጋምቤላና ቤንሻንጉል ጉምዝ ካላቸው ተፈጥሯዊ መስህብና አረንጓዴያማነት አኳያ ከእርሻ ይልቅ የኢኮ ቱሪዝም ሥራ ትኩረት ቢሰጠውና አዋጭነቱም ቢጠና በማለት ምክረ ሐሳብ አቅርበዋል፡፡ በመደበኛ ሥራቸው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የፕሮግራም ኦፊሰር የሆኑት አጥቅየለሽ (ዶ/ር)፣ የ20 ዓመታት የጥናትና ምርምር ተሞክሮ አካል የሆነውና ‹‹ፎሬን ዳይሬክት ኢንቨስትመንት ኢን ላርጅ ስኬል አግሪካልቸር ኢን አፍሪካ›› በሚል ርዕስ ያሳተሙት መጽሐፍ፣ ስድስት የተመረጡ እርሻዎች በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና አካባቢያዊ ዘላቂነት ላይ ያሳደሩትን ጫና በትንታኔ አቅርበውበታል፡፡ ", "passage_id": "52208f6f2b25a72d7de9d7955b33356d" }, { "passage": "ስምምነቱ 1.2 ቢሊዮን አፍሪካውያንን ተጠቃሚ እንደሚያደርግና ለሃገራት ኢኮኖሚ እድገት አስተዋፅኦ እንዳለው እየተነገረም ይገኛል።\n\nእንደ አውሮፓ ሕብረት ዓይነት ቅርፅ ይዞ ለመንቀሳቀስ እያሰበ ያለው ይህ ቀጣና በአፍሪካ ሃገራት መካከል ድንበር የማያግዳቸው የንግድ ልውውጦች እንዲካሄዱ እንደሚያዝ፤ አልፎም ግብር እና አስመጭዎች ላይ የሚጫነውን ቀረጥ በማስቀረት በአህጉሪቱ ሃገራት መካከል ያለውን ነፃ ዝውውር እንደሚያበረታታ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ያስረዳሉ።\n\nምንም እንኳ ኢትዮጵያን ጨምሮ 44 የአፍሪካ ሃገራት ስምምነቱ ይጠቅመናል ብለው ቢፈርሙም የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች የአፍሪካ ሃገራት በእኩል የዕድገት ደረጃ ላይ አለመሆናቸው ለማዕቀፉ ተፈፃሚነት ትልቅ እንቅፋት ነው ሲሉ ይሞግታሉ። \n\nከእነዚህም መካከል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍና ንግድ፣ ግብር፣ ፋይናንስና ኢንቨስትመንት መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ፍሰሃ-ፅዮን መንግሥቱ አንዱ ሲሆኑ ከስምምነቱ ቀድሞ መምጣት ያለበት ነገር እንዳለ ለቢቢሲ ይናገራሉ።\n\n\"በጠቅላላቅ የአፍሪካን ሆነ የኢትዮጵያን ገበያ ሳናሳድግ አንድ ማዕከላዊ ገበያ መመስረታችን ጥቅሙ ለማን ነው?\" በማለት ይጠይቃሉ ምሁሩ። ስምምነቱ ላይ ምንም ዓይነት ተቃውሞ እንደሌላቸው የሚያስረግጡት ፕሮፌሰር ፍሰሃ ከማዕቀፉ በፊት ሊሰሩ የሚገቡ በርካታ የቤት ሥራዎች እንዳሉ ይጠቁማሉ።\n\n\"ቪሳ እንኳን ለማግኘት ችግር በሆነበት አህጉር ይህ ስምምነት ላይ መድረስ ትንሽ ችኮላ የበዛበት ይመስለኛል። እንደእኔ አስተሳሰብ የኢትዮጵያ መሪዎች የኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅም የሚያስከብር ውሳኔ ነው መወሰን ያለባቸው። ለሃገራችን ተስማሚ ሆኖ ካልተገኘ አንቀበለም ማለት መቻል አለባቸው። ማንኛውም ስምምነት ሲደረግ መለኪያው መሆን ያለበት አሁን ላለው እንዲሁም ለመጪው ትውልድ ያለው በጎ አስተዋፅኦ ነው\" ባይ ናቸው ምሁሩ።\n\nነፃ የንግድ ቀጣናው ለኢትዮጵያዊያን አምራቾች የሚሰጠው ጥቅም ምንድነው? ጉዳቱስ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ፕሮፌሰር ፍሰሃ ምላሽ ሲሰጡ \"ለምሳሌ ኬንያን እንመልከት። በቴክኖሎጂ፣ ኢንዱስትሪና በሰለጠነ የሰው ኃይል ከኛ የተሻሉ ናቸው። ወደእኛ ሃገር መጥተው ንግድ የሚያከናውኑ ከሆነ በእርግጠኝነት የእነሱ ጥቅም እንጂ የእኛ ጥቅም አይከበርም። ለአምራቹም ጉዳቱ የሚያመዝ ነው የሚሆነው።\"\n\n\"መሆን ያለበት ለእኛ ከሚበጁ ጋር አብሮ መስራት እንጂ ሁሉንም እሺ ብለን የምንቀበል ከሆነ ዘላቂ የሆነ ጥቅም አናገኝም፤ የሃገራችን አምራቾችም አይጠቀሙም\" ይላሉ።\n\nየአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የወቅቱ ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት በበኩላቸው ስምምነቱን ''መልካም ፈተና\" ሲሉ ቢጠሩትም \"የስኬት ጥማት እንዲኖረንና ድፍረት እንድናዳብር ኃይል ይሰጠናል\" ብለዋል። ለስምምነቱ መሳካት የአህጉሪቱ ሃገራት ''ፖለቲካዊ ልዩነቶቻቸውን ማጥበብ ይኖርባቸዋል'' ሲሉም አሳስበዋል።\n\nየተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ምጣኔ ሃብት ኮሚሽን ስምምነቱን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ላይ ''በዚህ ስምምነት 80 በመቶ በሚሆነው የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳታፊ የሆኑት አነስተኛና መካከለኛ ተቋማት እንዲሁም 70 በመቶ መደበኛ ያልሆነ ድንበር ተሻጋሪ ንግድ ላይ የተሰማሩ ሴቶች እና ወጣቶች ዋነኛ ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ይላል። \n\nሆኖም ግን ናይጄሪያን ጨምሮ ሌሎች 10 የአፍሪካ ሃገራት ይህን ስምምነት ለመፈረም አልፈቀዱም። ስምምነቱ እውን እንዲሆንና ተፈፃሚነቱ እንዲረጋገጥ 54ቱም የአፍሪካ ሃገራት ፊርማቸውን ማሳረፍ ግድ ይላቸዋል።\n\n ", "passage_id": "1876af83ebaef258c66d206fe87cf957" }, { "passage": "በኢትዮጵያ እየተካሄደ የሚገኘው ለውጥ በርካታ የውጭ ኩባንያዎችን እየሳበ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።  የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ አበበ አበባየሁ እንደገለጹት በሀገሪቱ ለመሰማራት ፍላጎት እያሳዩ የሚገኙት የውጭ ኩባንያዎች የውጭ ንግድ አፈጻጸሙን ከፍ የሚያደርጉና በርካታ የስራ እድሎችን መፍጠር የሚችሉና የህዝቦችን የስራ ባህል የሚያሻሽሉ ናቸው ብለዋል።እንዲሁም የውጭ ኩባንያዎችን ለመቀበል የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ምቹ የማድረግ ስራም እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።በስፋት እየተከናወነ ከሚገኘው የፖለቲካ  ማሻሻያ ስራ ጎን ለጎንም የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ ቀጣይነት ባለው መልኩ የኢኮኖሚውን እድገት ማፋጠን እንደሚያስፈልግ ታምኖበት ኮሚሽኑ በከፍተኛ እንቅስቃሴ ላይ መሆኑንም ነው የተናገሩት።የኢኮኖሚ ማሻሻያው አላማም የሀገሪቱን ዕድገት በማስቀጠልና የህዝቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ለወጣቱ የስራ ዕድል ማስፋፋት መሆኑንም ጠቅሰዋል።እየተካሄደ ያለው ለውጥ ማህበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ መካሄዱም የውጭ ባለሃብቶች ከዚህ ቀደሙ በተሻለ መልኩ ፊታቸውን ወደ ኢትዮጵያ የማድረግ ፍላጎታቸውን እያሳዩ ነው ብለዋል ኮሚሽነሩ።በቅርቡ የጀርመኑ የቮልስ ዋገን ተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ በዘርፉ የመሰማራት ፍላጎት ማሳየቱን ተከትሎ የመግባቢያ ስምምነት መፈረሙን መከናወኑን አስታውሰዋል።በተመሳሳይም የአበባ አምራች ኩባንያዎች በአማራ ክልል ቁንዝላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሰፊ  ቦታ ወስደው ወደልማት እንዲገቡ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።እንዲሁም በኦሮሚያ እና በሌሎች ክልሎችም አዳዲስ የውጭ ባለሃብቶች በተለያዩ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት ማሳየታቸውን አንስተዋል።  (ምንጭ፡-ኤፍ.ቢ.ሲ)", "passage_id": "59eb0b47056a4fcd7aa04be06b139d9c" }, { "passage": " ከደርባ ሲሚንቶ በስተቀር ከግሉ ዘርፍ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ብድር ወስዶ የሚሰራ ድርጅት እንደሌለ የተገለፀ ሲሆን፣ ባንኩ ከግል ኢንቨስተሮች ጋር ለመሥራት ፈቃደኛ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ም/ፕሬዚዳንት፤ የግል፣ የመሰረተ ልማትና የኢንዱስትሪ ዘርፍ ኃላፊ ሚ/ር ፒየር ጉስሌይን፣ በኢትዮጵያ ለ3 ቀን ያደረጉትን ጉብኝት አስመልክተው ባለፈው ማክሰኞ በራዲሰን ብሉ ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ከመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት፣ ከኢንዱስትሪና ከንግድ ሚኒስትሮች ጋር፣ እንዲሁም የግል ዘርፉን ጨምሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ያደረጉት ውይይት ፍሬያማ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ ሚ/ር ጉስሌይን፤ ድርጅታቸው በ2001 ዓ.ም ለደርባ ሲሚንቶ 55 ሚሊዮን ዶላር ያበደረ ብቸኛው የግል ባንክ መሆኑን ጠቅሰው፣ ደርባን ሲሚንቶን ሲጎበኙ፣ ጥራት ባለው እንቅስቃሴውና ለአህጉሩ የኢኮኖሚ ዕድገት በሲሚንቶ አቅርቦት እያደረገ ባለው አስተዋጽኦ መርካታቸውን ገልፀዋል፡፡ ሌሎች የግል ኢንቨስተሮች ከባንኩ ጋር የማይሰሩትና የማይበደሩት፣ ባንኩ፣ ለግሉ ዘርፍ እንደሚያበድር ግንዛቤው ስለሌላቸው እንደሆነ ጠቅሰው፣ “በተለይ በኤክስፖርት ዘርፍ ከተሰማሩ የግል ኢንቨስተሮች ጋር ለመስራት ገንዘብ አዘጋጅተን እየተጠባበቅን ነው፤ ኑ አብረን እንሥራ!” በማለት ጋብዘዋል፡፡ ም/ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያ ስላደረጉት ጉብኝት በሰጡት መግለጫ፣ ተደጋጋሚ ድርቅ፣ ዓለም አቀፍ የምርት ፍላጎት መቀነስና የሸቀጦች ዋጋ መውደቅ ቢያጋጥማትም፣ ኢትዮጵያ ጠንካራና እውነተኛ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒ) ዕድገት ስላሳየች፣ የትራንስፎርሜሽን እቅዷን ታሳካ ዘንድ ባንኩ፣ በኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ “ባንኩ፣ ለአፍሪካ ያለው አመለካከት፣ ቅድሚያ በሚሰጣቸው አምስት ስትራቴጂዎች ይጠቃለላል” ያሉት ሚ/ር ጉስሌይን፣ “እነሱም፣ አፍሪካን የመብራትና የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ፣ አፍሪካን መመገብ፣ አፍሪካን በኢንዱስትሪ ማበልጸግ፣ አፍሪካን አንድ ማድረግና የአፍሪካን ህዝብ ኑሮ ጥራት ማሻሻል ነው” ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር መስራት የጀመረው ከ42 ዓመት በፊት በ1975 ሲሆን እስከ አሁን ወጪያቸው በአጠቃላይ 4.6 ቢሊዮን ዶላር የሆነ 130 ፕሮጀክቶች (በመሰረተ ልማት፣ በኃይል፣ በውሃና ሳኒቴሽን) በማህበራዊ፣ በእርሻና በግሉ ዘርፍ ተከናውነዋል፡፡ ባንኩ፣ በአሁኑ ወቅት በ2 ቢሊዮን ዶላር 26 ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑ ታውቋል፡፡ ባንኩ፣ ከኢትዮጵያ ጋር ባለው ተሳትፎ አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የጠቀሱት ም/ፕሬዚዳንቱ፤ ኢትዮጵያና ጅቡቲን ለሚያገናኘው ስትራቴጂያዊ የኃይል አቅርቦት፣ ኢትዮጵያ - ኬንያን ለሚያገናኘው የመንገድ ፕሮጀክት፣ ለገጠር የኤሌክትሪክ አቅርቦትና መቀሌን ከዳሎል ለሚያገናኘው የኃይል ማሰራጫ መስመር፣ ባንኩ፣ 900 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስት ማድረጉን ተናግረዋል። እንዲሁም ባንኩ፣ የምስራቅ አፍሪካን የኃይል ፕሮጀክት እየደገፈ ነው፡፡ እነዚህ ተግባራት፣ የገጠርና የከተማ ቤቶች፣ የኢንዱስትሪ ዞኖች፣ የማዕድን ማዕከላት ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ማስቻል፣ አፍሪካን ብርሃናማ ማድረግና ለአፍሪካ ኃይል (ፓወር አፍሪካ) ቅድሚያ መስጠት ይሆናል ተብሏል፡፡ አፍሪካን አንድ ማድረግ ወይም ማስተሳሰር በሚለው የባንኩ ስትራቴጂ፣ በትራንስፖርት ዘርፍ አገራዊና አኅጉራዉ ትስስርን ለመፍጠር ለምሳሌ የኢትዮ - ኬንያ ትራንስፖርት ኮሪደር ፕሮጀክት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድና የቦሌን አለም ዓቀፍ አየር ማረፊያ ደረጃ ለማሳደግ፣ ለበርካታ መንገዶች መገንቢያና ማደሻ፣ ባንኩ አንድ ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት ማድረጉ ታውቋል፡፡ የእርሻውን ዘርፍ ለመደገፍና ለማዘመን፣ 7, 000 ሄክታር የሚሸፍነውንና 77 ሚሊዮን ኪዩቢክ የመያዝ አቅም ያለውን የካጋ መስኖ ፕሮጀክት፣ በእርሻው ዘርፍ ዝናብ ላይ የሚታየውን ጥገኝነት ለመቀነስና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ባንኩ ለኢትዮጵያ 630 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ማድረጉ ታውቋል። እንዲሁም የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ አቅም ለማጎልበት በተለይም በሲሚንቶ ምርትና በማዕድን ዘርፍ 160 ሚሊዮን ዶላር በብድር ተሰጥቷል፡፡ እንዲሁም ባንኩ፣ ለውሃ አቅርቦትና ለሳኒቴሽን 340 ሚሊዮን ዶላር፣ ለበጀት ድጎማ፣ ለማኅበራዊ አገልግሎት፣ ለትምህርት፣ ጤናና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማሻሻልና ለመደገፍ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት ማድረጉ ተገልጿል፡፡ ", "passage_id": "322816121727c9b00b1504daa4ab32e5" }, { "passage": "ባለፉት ሁለት ዓመታት በተካሄደ ጥናት መሠረት የአሜሪካ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ የኢንቨስትመንትና የንግድ መስኮች፣ ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት ማድረጋቸው ተገለጸ፡፡የኧርነስት ኤንድ ያንግ ማኔጂንግ ፓርትነር አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ይህን ያስታወቁት ለአሥረኛ ጊዜ የአፍሪካ ኮርፖሬት ምክር ቤት የተባለ መቀመጫውን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው ድርጅት፣ በአዲስ አበባ እያካሄደው ባለው የአሜሪካና አፍሪካ የንግድ መድረክ ስብሰባ ወቅት ነው፡፡የአሜሪካና የአፍሪካ የንግድ መድረክ ከጥር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ሲሆን፣ መድረኩን በይፋ የከፈቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ናቸው፡፡ በመክፈቻ ንግግራቸው የአሜሪካ ባለሀብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን በአኅጉሪቱ እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪ ከአሜሪካ ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የኢንቨስትመንት ምኅዳሩን የተመቻቸ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን፣ በተለይም የቴሌኮም አገልግሎቱን እንደምታሻሽል ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የአሜሪካ ባለሀብቶች ከማዕድናት ዘርፍ በተጨማሪ በጨርቃ ጨርቅ፣ በቆዳ፣ በግብርናና በግብርና ማቀነባበሪያ፣ በታዳሽ ኃይል፣ በመንገድና በባቡር መስመር ዝርጋታዎች ቢሳተፉ የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ለተሰብሳቢዎቹ አስረድተዋል፡፡የአፍሪካ ኮርፖሬት ምክር ቤት እንዲህ ዓይነት ስብሰባ በሁለት ዓመት አንዴ የሚያካሂድ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም አኅጉሪቱን ከአሜሪካ ኢንቨስተሮች ጋር በማገናኘት ቢዝነስና ኢንቨስትመንት እንዲጠናከር የሚያደርግ ድርጅት ነው፡፡ይህ ስብሰባ ኢትዮጵያ ውስጥ መካሄዱ ትልቁ አንድምታ አለው ያሉት አቶ ዘመዴነህ፣ ‹‹አሜሪካኖች ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ለማድረግ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ትኩረት እንደተሰጠው የሚያሳይ ነው፤›› በማለት፣ የሁለቱ አገሮች ግንኙነት ቀደም ሲል ይታወቅበት ከነበረበት የደኅንነትና አካባቢውን የማረጋጋት ሥራ ባሻገር ወደ ኢንቨስትመንትና ኢኮኖሚ መስክ መሸጋገሩን የሚያሳይ እንደሆነ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡በዚህም መሠረት ባለፉት ዓመታት ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የኢንቨስትመንት መጠን ከፍተኛ እንደሆነ አስታውሰው፣ የአገሪቱ ትልልቅ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ መዋዕለ ንዋያቸውን እያፈሰሱ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ከእነዚህም መካከል የኮርቤቲ ጂኦተርማል ፕሮጀክት፣ ከጂቡቲ ወደ ኢትዮጵያ የሚዘረጋው የነዳጅ መስመር ማስተላለፊያ መስመር፣ የጄኔራል ኤሌክትሪክ አነስተኛ ፋብሪካ ለመሥራት መፈለግ፣ እንዲሁም በ250 ሚሊዮን ዶላር የሚካሄደው የኮካ ኮላ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የአገሪቱና የአሜሪካ ግንኙነት እየተጠናከረ ለመምጣቱ ማሳያ ነው በማለት አብራርተዋል፡፡አሁን ከመጡትና መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ ከጀመሩት ኩባንያዎች በተጨማሪ፣ የኢትዮጵያ ገበያ ውስጥ ለመግባት በዝግጅት ላይ ያሉ ድርጅቶች እንዳሉ የገለጹት አቶ ዘመዴነህ፣ ‹‹ምንም እንኳን በአሁኑ ጊዜ ስማቸውን መግለጽ ባልችልም በመጪው ዓመት ከመንፈቅ ውስጥ ግን የሚፈረሙ ስምምነቶች ይኖራሉ፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡በዚህ ለአራት ቀናት በአዲስ አበባ የሚካሄደው የንግድና ኢንቨስትመንት መድረክ ላይ ከ1,200 በላይ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡ በስብሰባ መድረኩ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሊንዳ ቶማስ ግሪን ፊልድን ጨምሮ፣ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ኮሳዛና ድላሚኒ ዙማ፣ እንዲሁም የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሥራ አስፈጻሚዎችና ኃላፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ ", "passage_id": "e6af84c457cfbc0db6d9b25ed752bf8c" } ]
6291b068151e380611c3bf855dc13b0a
77e6b9a3e2eb3d0b60f6a05d6f400d79
የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችን ለመጀመር ብቻ ሳይሆን ለመጨረስ ታስቦ ወደሥራ እንደሚገባ ተገለጸ
አዲሱ ገረመውአዲስ አበባ፡- የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች እንደ ሸገር ፕሮጀክቶች ሁሉ መጀመርን ሳይሆን መጨረስን ታሳቢ በማድረግ ወደ ሥራ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ። ክልሎችም ሆኑ በፕሮጀክቱ ላይ የሚመደቡ አመራሮችና ባለሙያዎች ይህንኑ ታሳቢ አድርገው እንዲሠሩም አሳስበዋል። የሦስቱም የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች (ወንጪ፣ ጎርጎራና ኮይሻ) አስተባባሪዎች የፕሮጀክቶቹን አጠቃላይ ገጽታ አስመልክተው ትላንት ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ በተገኙበት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚህ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሊጀመሩ በታቀዱ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች ላይ ሰፊ የልማት ፍላጎት መታዩትን ገልጸው፤ ነገር ግን ፍላጎትን ከአቅም ጋር ማጣጣም እንደሚገባ እና ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ እንደተከናወነው ከተማን የማስዋብ ሥራ ሁሉ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችም መጀመርን ሳይሆን መጨረስን ታሳቢ አድርገው ሊሠሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፤ ሁል ጊዜ ሥራን ከትንሽ በመጀመር በፍጥነት በማሳደግ የሚፈለገውን ትልቁን ነገር ማግኘት እንጂ የመሠረት ድንጋይ በማስቀመጥ ያልተፈጸመበትን ምክንያት ማቅረብ አይደለም። በዚህም መሠረት የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት በሦስቱ ክልሎች (በኦሮሚያ፣ አማራና ደቡብ) እንደሚከናወኑ ተወስኗል። ፕሮጀክቶቹ ለሌሎች ልማቶች ሳቢ በሆነ መንገድ የሚሠሩ ይሆናሉ።በሦስቱም አካባቢዎች የፕሮጀክቶቹን ዓላማ በትክክል ያለመገንዘብና የማስፋት ፍላጎት ይታያል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይሄ ፕሮጀክት በክልልም ይሁን በፌዴራል መንግሥት በጀት ሳይሆን ህዝብን በማስተባበር እንደሚሠራ አመልክተዋል። የፕሮጀክቱ ዋነኛ ዓላማም በአዲስ አበባ የተከናወነውን ከተማን የማስዋብ ሥራ በየክልሉ በተመረጡ ቦታዎች ላይ ማዳረስ ሲሆን፤ አስተባበሪዎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ሃሳባቸውን ሰውተው በመሥራት የግሉ ሴክተር እንዲስፋፋ የበኩላቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ፕሮጀክቶቹ ተጀምረው እስከሚያልቁ የፌዴራል መንግሥት ፕሮጀክቶች እንጂ የክልሎች ፕሮጀክቶች አይደሉም። ሥራውን በማስኬድ  ሂደት የክልል ጣልቃ ገብነትም አይፈልግም። ነገር ግን ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። የፌዴራል መንግሥት ሥራውን ሲጨርስም ያስረክባቸዋል። ይህን ከወዲሁ ለሙያተኞች ማስገንዘብም ከአመራሮች ይጠበቃል። በገንዘብ አሰባሰብ ሂደቱ ከፌዴራል መንግሥት የመጠበቅ ዝንባሌዎች እንዳሉና ነገር ግን በፌዴራል መንግሥት የተለየ የገንዘብ ምንጭ ስለሌለ በዚህ ፕሮጀክት እሳቤ መሠረት ህዝብን የማስተባበር ሥራ እንደሚሠራ ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚያስፈልግም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። በተጨማሪም ገንዘብ ሲሰበሰብ አንዳንድ ቦታ የተሳካ፣ አንዳንድ ቦታ ላይ ደግሞ ያነሰ ሊሆን ስለሚችል ገንዘቡ ሌላውንም ፕሮጅክት የልማት አካል አድርጎ ማሰብ ያስፈልጋል ብለዋል። በዚህም አጠቃላይ ገቢው ወደ ማዕከል ከገባ በኋላ የሚከፋፈል እንጂ አንዱ ክልል ያዋጣው ለክልሉ ብቻ እንደማይሆንም ጠቅሰዋል። የፕሮጀክቱ ሥራ መጀመርን ሳይሆን መጨረስን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆንም በዚህ ሥራ ውስጥ በፌዴራል በተመደቡ የፕሮጀክት ኃላፊዎች ውጪ ክልሎች መመደብ እንደማይችሉ አሳስበዋል። የገበታ ለሀገር ሦስቱ ፕሮጀክቶች የዲዛይንና የደረሱበት ሂደት በአስተባ ባሪዎች ገለጻ ተደርጎ ውይይት ተካሂዶበታል። በውይይቱ ላይ የገበታ ለሀገር ሦስቱ ፕሮጀክቶች የሚከናወኑባቸው ክልሎች ርዕሰ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮች እና የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 8/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37508
[ { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕሮጀክቶች አስተዳደራዊ አፈጻጸም በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ ምክንያት በ4 ቢሊየን ብር የተጀመሩ ፕሮጀክቶች እስከ 16 ቢሊየን የሚጠጋ ብር እንደሚጨርሱ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈጥሮ ሀብት፣ መስኖና ኢነርጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ።ቋሚ ኮሚቴው የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርንና የተጠሪ ተቋማቱን የ2013 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡በግምገማው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተጠሪ ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ በመስራትና  ቋሚ ኮሚቴው የሚሰጣቸውን ግብረ መልሶች በግብአትነት ከመጠቀም እንዲሁም፤ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ወቅታዊ አደጋዎችና ችግሮችን ታሳቢ አድርጎ ከማቀድ አኳያ ውስንነት እንዳለበት ቋሚ ኮሚቴው በዝርዝር አንስቷል፡፡ከአፈፃፀም ዝቅተኛ መሆን ባሻገር አብዛኛዎቹ መሰረተ ድንጋይ ከማስቀመጥ ያለፈ ተጠናቀው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ሲያደርጉ አለመታየቱን የቋሚ ኮሚቴው አባላት አስረድተው በቀጣይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ለውሃ ልማት ፈንድ የሚሰጠው ተዘዋዋሪ ብድር እንዲመለስ በተደጋጋሚ ቢጠየቅም ባለመመለሱ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንቅፋት መሆኑን የጠቆመው ቋሚ ኮሚቴው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚገነቡ ንዑስ ጣቢያዎች የመብረቅ መከላከያ ባለመሰራቱ አብዛኛዎቹ ከሳምንት በላይ እያገለገሉ አለመሆኑም ተነስቷል።በመሆኑም በ2013 በጀት ዓመት ችግሩ ታሳቢ ተደርጎ መፍትሄ ሊቀመጥለት እንደሚገባ ቋሚ ኮሚቴው መግለፁን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡", "passage_id": "44bfd78894ddf70b0deed8b2bada2af7" }, { "passage": "የዐፄ ምኒሊክ የግብር አዳራሽ\n\n'ገበታ ለሸገር' በሚል ስያሜ የተዘጋጀው የገንዘብ ማሰባሰቢያ የእራት ዝግጅት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድና ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት የሚታደሙበት ሲሆን በዝግጅቱ ላይ ለመገኘት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተሳታፊዎች የተለያየ መታሰቢያ መዘጋጀቱ ተነግሯል። \n\n• የ5 ሚሊዮን ብር እራት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ጋር\n\nዛሬ የሚከናወነው 'ገበታ ለሸገር' የእራት ዝግጅት ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች የሚጀመር ሲሆን ከዋናው የእራት ግብዣ ቀደም ብሎ የተለያዩ ግንባታዎችና ጥገና እየተካሄደበት የሚገኘው የጠቅላይ ሚኒስትሩ መንበር የሚገኝበት ታሪካዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ የሚደረግ ጉብኝት እንደሚኖር ታውቋል።\n\nበጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የ'ገበታ ለሸገር' የ5 ሚሊዮን ብር እራት ላይ ለመገኘት ከተመዘገቡ እንግዶች መካከል በተለያዩ ዘርፎች ላይ የተሰማራው የቢኬ ግሩፕ (በላይነህ ክንዴ ግሩፕ) ባለቤት አቶ በላይነህ ክንዴ እንዱ ናቸው።\n\n\"ገበታ ለሸገር የልማት ሥራ ነው፤ እንደ አንድ ባለሃብት የአፍሪካ መዲና፣ የዓለም መሰብሰቢያ የሆነችው ሸገር እንድትዋብ እንዲትለወጥ ፍላጎታችን ነው\" የሚሉት አቶ በላይነህ ዓላማውን በመደገፍ ያለምንም ማመንታት ገንዘቡን እንደከፈሉ ይናገራሉ። እራቱ ላይም ይህንን ዓላማ ለማስተዋወቅ እንደሚገኙ ገልፀው \"በአጋጣሚውም እራታችንን እንጋበዛለን\" ብለዋል።\n\n• የማትተነፍሰው ከተማ: አዲስ አበባ\n\n\"ምግብ ለመመገብ አይደለም የምንሄደው\" የሚሉት አቶ በላይነህ \"ሃብት ያለው ሰው በሕብረት ሌሎች ከተሞችንም ካለማ አገር ያድጋል\" የሚል ሃሳብ አላቸው። የዚህ እራት ዓላማውም የልማት ነው ሲሉ አክለዋል።\n\nየፕሮግራሙ ዝርዝር ባይደርሳቸውም ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት እንዲገኙ የግብዣ ወረቀት ደርሷቸዋል። በፕሮግራሙም ላይ ተገኝተው በሚኖረው መርሃግብር ላይ እንደሚሳተፉ ነግረውናል።\n\nየወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የሚኖረው ገጽታ\n\nሌሎች የአፍሪካ ከተሞችን እንዳዩና በጽዳት የተሻሉ እንደሆኑ በቁጭት የሚናገሩት አቶ በላይነህ \"አገር በግለሰብ ለማልማት ሊሞከር ይችላል፤ እንደዚህ በጋራ ሆኖ ማልማት ጠቃሚ ነው\" በማለት ይህንን ዓላማ እንደደገፉ ገልጸዋል። \n\nየእራት መስተንግዶውም በቤተ መንግሥቱ ውስጥ በሚገኘው በታሪካዊው የአፄ ምኒልክ የግብር አዳራሽ ውስጥ እንደሚካሄድ የተነገረ ሲሆን እስካሁን ከሁለት መቶ በላይ ግለሰቦችና ተቋማት በእራት ድግሱ ላይ በመታደም አስተዋጽኦ ለማበርከት መመዝገባቸው ተነግሯል። \n\n• ''አዲስ አበባ የሁላችንም ከተማ ናት'' ከንቲባ ታከለ ኡማ \n\nሸገርን የማስዋብ ዕቅድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አነሳሽነት የተጀመረ የሦስት ዓመታት ፕሮጀክት ሲሆን በዚህም ከእንጦጦ እስከ አቃቂ የሚዘልቅ የ56 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍን በወንዝ ዳርቻዎች አካባቢ የሚገኙ ስፍራዎችን ለማልማት የታቀደ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። \n\nየታቀደው የአዲስ አበባ የወንዞችና የወንዞች ዳርቻን የማልማት ዕቅድ ተግባራዊ ሲሆን በተለያዩ የፕሮጀክቱ ሥፍራዎች ላይ በእራት ዝግጅቱ የታደሙ ሰዎች ስም በተናጠል ተጽፎ የሚቀመጥ ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ጋርም የአንድ ለአንድ ፎቶ የመነሳት እድልን ያገኛሉ ተብሏል።\n\nይህም ፎቶግራፍ የአዲስ አበባን ገጽታ የቀየሩ ግለሰቦች በሚል ተሰባስቦ በአንድ ጥራዝ ላይ እንዲቀርብ ይደረጋል ተብሏል።\n\nበጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ 'ገበታ ለሸገር' ላይ ከሚሳተፉት ሰዎች አንዱ የሆኑት አቶ በላይነህ ክንዴ \"እንደ ግለሰብ፤ 5 ሚሊዮን ብር ስለከፈልኩ በእኔ ስም ቦታ ይሰየምልኝ ብዬ አላስብምም፤ መሆንም የለበትም፤ ስሜን ለማስተዋወቅ አይደለም... ", "passage_id": "f0fe6181b68bdaa10c07808339ff1a8f" }, { "passage": "ለግንባታው የሚያስፈልገውን ገንዘብ ለማሰባሰብ የሚያግዙ ስልቶችን ቀይሶ እየሠራ መሆኑን ጽሕፈት ቤቱ አስታውቋል፡፡የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የሚዲያ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ኃይሉ አብርሃም እንዳስታወቁት የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ዘዴዎችን ተግባራዊ በማድረግ 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታልሞ እየተሠራ ነው፡፡በክብርት ፕሬዝዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ በቅርቡ ይፋ የሆነው ሦስተኛው ዙር የ8100 A የተንቀሳቃሽ ስልክ የጽሑፍ መልዕክት ከገቢ ማሰባሰቢያ ዘዴዎች አንዱ ነው፡፡ በዚህም እስከ 20 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል፡፡ ከዚህ በፊት ተዘርግተው በነበሩት የ8100 A የተንቀሳቃሽ ስልክ የጽሑፍ መልዕክት የገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብሮች 130 ሚሊዮን ብር ተሰብስቦ ገቢ መደረጉም ታውቋል፡፡", "passage_id": "aad45c20e6565d9939de761a6a158a5d" }, { "passage": "በአገር ውስጥ ግንባታቸው እየተካሄዱ ያሉትን የአስር ግድቦችን የግንባታ ሥራ ለማጠናቀቅ በ50 ቢሊየን ብር በጀት ለመጠናቀቅ ርብርብ እየተካሄደ መሆኑን የውሃ ፣መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር አስታወቀ ።\nሚንስትር ዲኤታው አቶ ከበደ ገርባ ለዋልታ እንደገለጹት በ50 ቢሊዮን ብር ወጪ  ግንባታቸው  እየተከናወኑ ያሉትን  የ10 ግድቦችን ግንባታ  በማፋጠን  እስከመጪው ዓመት መጨረሻ ጊዜ  ለማጠናቀቅ እየተሠራ  ይገኛል ።በግንባታ ላይ ከሚገኙት 10 ግድቦች መካከል ተንዳሆና ከሰም ግድቦች ግንባታቸው ሙሉ በሙሉ  ተጠናቆ  የመስኖ ሥራውን ለማስጀመር የሚያስችላቸው ቅድመ ሥራዎች እየተካሄዱ   መሆኑን  አቶ ከበደ ተናግረዋል ።የመገጭ ፣ የርብና የጊዳቦ የመስኖ ግድቦችም ከማጠናቀቂያ ሥራዎቻቸው በስተቀር  ግንባታው መጠናቀቁንና የአምስት  ግድቦቹ ግንባታም በመጪዎቹ  ዓመት ለማጠናቀቅ  የግንባታ ሥራዎች  እየተፋጠኑ መሆኑን  አቶ ከበደ አብራርተዋል።እንደ ሚንስትር ዲኤታው ገለጻ በዲዛይን መቀያየር ምክንያት የግንባታ ጥራት መጓደል ፤  የግንባታ ሥራዎች አለመፋጠን ምክንያት የሚያጋጥሙ ወጪ መጨመር በዘርፉ  ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ናቸው ።የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ሚንስትር ዲኤታው አቶ ተስፋዬ  በበኩላቸው በመላ አገሪቱ  በ 2ነጥብ4  ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የመካከለኛና አነስተኛ የመስኖ ሥራዎች እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።በዘንድሮ የበጀት ዓመት በመካከለኛና በአነስተኛ መስኖ ልማት የሚሸፈነው መሬት 3 ሚሊዮን  ሄክታር ለማድረስም የሚያስችሉ ሥራዎች እየተካሄዱ መሆኑን አቶ ተስፋዬ አያይዘው ገልጸዋል ።በቀጣይም የግንባታ ሥራቸው  ያልተጠናቀቁት የመስኖ ግድቦች ሥራ  ሲጠናቀቅ  በአገሪቱ በመስኖ  ልማት  ደረጃው  ከፍ  ያደርገዋል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል ።                        ", "passage_id": "ece3a4172d0a60f316adace4e55bfb09" }, { "passage": "ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ለ\"ሸገርን ማስዋብ\" ፕሮጀክት ገንዘብ ከሚያሰባስበው የ\"ገበታ ለሸገር\" አስተባባሪ ኮሚቴ ጋር ውይይት አደረጉ።ከኮሚቴው ጋር ትልንት ከሰዓት በኋላ ተገናኝቶ ስለደረሰበትን ደረጃ ውይይት ያሄደ ሲሆን  እጁ ላይ ያለውን ሥራ አጠናቆ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውጤቱን ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል ተብሎም ይጠበቃል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአዲስ አበባ ስራው በይፋ ለተጀመረው ሸገርን ማስዋብ ፕሮጀክት የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ምሽት ማዘጋጀታቸው የሚታወስ ነው፡፡በእራት ምሽቱ ዲፕሎማቶች፣ የኩባንያ ስራ አስኪያጆች፣ የአለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች እና ሎሎች አካላት እንዲሳተፉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።ሸገርን ማስዋብ ፕሮጅክት በሚል የ29 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ መደረጉ የሚታወስ ነው።ከተማዋን ለሁለት ከፍለው የሚፈሱ ወንዞች ላይ ያተኮረው ፕሮጀክቱ ከሰሜን አዲስ አበባ እንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ወንዝ ያለውን 56 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍንም ታውቋል።ፕሮጀክቱ በ3 አመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። (ምንጭ፡-ጠቅላይ ሚንስትር ጽህፈት ቤት)", "passage_id": "2ab97d42ed7ee9cd021db9e072782d8e" } ]
5b2ed9efed9fa89cad1402051503e297
7f6ad3383ff2134d163bb9a69afdd62d
በኢትዮጵያ የተስተካከለ የግብርና ልማት ፖሊሲ ባለመቀረፁ ዘርፉ ስኬታማ ሳይሆን መቆየቱ ተገለጸ
አብርሃም ተወልደ አዲስ አበባ፡- የተስተካከለ የግብርና ልማት ፖሊሲ ባለመነደፉ እና ዕድገትን ከማፋጠን ይልቅ የማደናቀፍ ሚና የሚጫወቱ ፖሊሲዎች ሥራ ላይ በመዋላቸው በኢትዮጵያ ግብርናው ውጤታማ እንዳይሆን መደረጉ ተገለጸ።በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የተፈጥሮ ሀብት አያያዝ ምርምር ዳይሬክተር ዶክተር ተመስገን ደሳለኝ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እንደገለጹት፤ የግብርና ምርትና ምርታማነት ባለማደጉ የተነሳ በምግብ ራሳችንን መቻል አቅቶን በየዓመቱ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ወገኖቻችን የምግብ ዕርዳታ ለመጠየቅ ተገድደናል።ለዚህ ደግሞ በዘርፉ የነበረው የእድገት ውስንነት አንዱ ምክንያት ሲሆን፤ በዚህም እንደማነቆ ከነበሩ ጉዳዮች ውስጥ የበጀት ማነስ፣ የሰው ኃይልንና መሬትን አቀናጅቶ አለመጠቀም እና አርሶ አደሩ የሚጠቀምባውን የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችና ግብዓቶች በቀላሉ አለመገኘት ዋና ዋናዎቹ መሆናውንም ዶክተር ተመስገን ጠቁመዋል።የባለሙያው እውቀት ማነስ አንዱ ተግዳሮት መሆኑን የሚገልጹት ዳይሬክተሩ፤ አሁን ላይ ከዩኒቨርሲቲ ከሚወጣው ባለሞያ ይልቅ የአርሶ አደሩ እውቀት ልቆ ሄዷል ብለዋል። ይህም ለግብርናው የተሰጠውን ትኩረት ያክል ለዘርፉ ትምህርት እንዳልተሰጠ ማሳያ ነው ሲሉ ጠቁመዋል።እንደ ዶክተር ተመስገን ማብራሪያ፤ ተማሪውም የግብርናን ትምህርት የሚመርጠው መጨረሻ ላይ ነው። ሥራም ስለማያገኝ ግብርናን የሚመርጠው ተማሪ በአቅሙ አነስ ያለ ነው። በዚህም ምክንያት አርሶ አደሩን የመደገፍ አቅሙ እያነሰ መጥቷል። ስለዚህ መንግሥት እዚህ ላይ ትኩረት መደረግ አለበት። ከዚህ በተጓዳኝ ሊታረስ ከሚችለው መሬት አርባ በመቶ ወይም ሦስት ሚሊዮን ሄክታር መሬት አሲዳማ አፈር መሆኑን የሚናገሩት ዶክተር ተመስገን፤ ከዚህ ውስጥ 10 በመቶውን እንኳ ማከም አልተቻለም ብለዋል። ነገር ግን ከዚህ ውስጥ ስንዴ የሚበቅልባቸውን ቦታዎች ብቻ እንኳን በኖራ ብናክም ከውጭ የምናስገባውን ስንዴ በ50 በመቶ መቀነስ እንደሚቻል ዶክተር ተመስገን ጠቁመዋል።ዶክተር ተመስገን ጨምረው እንደገለጹት፤ በአሁኑ ጊዜ በመንግሥታዊ የምርጥ ዘር ድርጅቶች ብቻ በዓመት ከአንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸው ምርጥ ዘሮች ለአርሶ አደሩ እየቀረቡ ይገኛል። ማህበራትና አርሶ አደሩ እርስ በእርስ የሚለዋወጡት ሲጨመር መጠኑ ከሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ይሆናል። ይህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው እና መንግሥት ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ከሚወስዳቸው ዕርምጃዎች አንዱ ማሳያ ቢሆንም፤ ግብዓት በሚፈለግበት ሰዓት የማይደርሰበት ሁኔታ አለ።ዶክተር ተመስገን እንደሚሉት፤ በርካታ ጥናቶች በመስኖ፣ በእንስሳት እርባታ እና መኖ በመሳሰሉት ተሠርተዋል። አብዛኞቹ ደግሞ ችግር ፈቺዎች ቢሆኑም ተግባር ላይ አልዋሉም። ስለዚህ ባለሀብቱም ይሁን መንግሥት መዋለ ነዋይ በማፍሰስ እነዚህን ጥቅም ላይ ማዋል ቢቻል ብዙ ችግሮችን ማቃለል ይቻላል።በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ለመስኖ ልማት የሰጠችው ትኩረት አናሳ በመሆኑ በዚህ ዘርፍ ግብርናውን ለማሳደግ እንዳልተቻል ዶክተር ተመስገን ይገልጻሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ የከርሰ ምድር ውሃን ሳይጨምር ወደ 123 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር የሚጠጋ የውሃ ሀብትና ከ36 ሚሊየን ሄክታር በላይ ሊለማ የሚችል መሬት አለ የሚሉት ዶክተር ተመስገን፤ በሰብል የለማው የአገሪቱ መሬት ደግሞ 16 ሚሊየን ሄክታር ብቻ እንደሆነና ከዚህ ውስጥም በመስኖ ልማት የለማው መሬት 1 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታሩ ብቻ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=37512
[ { "passage": "ከውጭ የሚገባውን የስንዴ ምርት በአራት አመት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ በሃገር ውስጥ ለመሸፈን የሚያስችል እቅድ ተዘጋጀ።ግብርና ለተመዘገበው ሀገራዊ እድገት ትልቅ ድርሻ ቢያበረክትም እድገቱን ግን ማፋጠን አልተቻለም።ከዝናብ ጥገኝነት ያልወጣው ይህ ዘርፍ የመካናይዜሽን ትኩረት ማጣት፣ የምርምር ውጤቶች አናሳ መሆንና ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ሌሎች ተግዳሮቶች ብዙም እንዳይራመድ አድርገውታል።የግብርና ሚኒስቴር ዘርፉ አሁንም ድረስ ከግብዓት አቅርቦት አንጻር እንኳን ተመጣጣኝ አለመሆኑን፥ የምሁራን ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ በሚል መሪ ቃል መካሄድ በጀመረው መድረክ ላይ ገልጿል።የግብርና ሚኒስትር ዲኤታው አቶ ሳኒ ረዲ ከማዳበሪያ አንጻር በሄክታር የሚገባውን ያህል መጠቀም አለመቻሉን ይናገራሉ።ይህም ቢሆን ግን በዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ልማት አያያዝና አጠቃቀም 3 ነጥብ 6 ሚሊየን ተፋሰሶችን ለማዘጋጀት ታቅዶ ከእጥፍ በላይ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።በዘንድሮው የምርት ዘመንም ከ374 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ከዋና ዋና ሰብሎች ለማግኘት በቂ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።የአነስተኛ አርሶ አደሮችን ማሳ በመስኖ ለማልማት ከታቀደው የ1 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት ውስጥም ከእቅድ በላይ ማልማት መቻሉንም ከሚኒስቴሩ የተገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ።በመድረኩ ምሁራኑ የኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ በርካታ ሊሻገራቸው በሚገቡ ተግዳሮቶች ዙሪያ እንደሚገኝና ከዛ መውጣት እንደሚገባው ጠቁመዋል።የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ኡመር ሁሴን በበኩላቸው በተለይ ቴክኖሎጂን ለመጠቀምና ዘመናዊ የእርሻ ስርአትን ለመከተል በርካታ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመው በአንዳንዶቹም ወደ ተግባር መገባቱን አንስተዋል።ከምሁራን የሚገኙ ምሁራዊ ምክሮችን ለመጠቀም ይሰራል ያሉት ሚኒስትሩ፥ ይህ ውጤታማነቱ እየተረጋገጠ ሲሄድ ምርታማነትን እንደሚያሳድግ ጠቅሰዋል።እንደ እቅድ የተያዘውም እስከ 4 አመት ባለው ጊዜ ውስጥ አሁን ሀገሪቱ ከውጭ የምታገስገባውን የስንዴ ምርት በሀገር ውስጥ መሸፈን ነው።ሚኒስትሩ ይህን ውጤታማ ለማድረግ የሰነድ ዝግጅቶችን ጨምሮ መሰረታዊ ስራዎች መጀመራቸውን ጠቅሰው፥ በሰነዱ ላይ በየደረጃው ውይይት ከተደረገበት በኋላ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል።የግብርና ሚኒስቴር አሰራሩን በአዲስ መልክ እየፈተሸ ያሉበትን ችግሮች እየፈታ ዘርፉ የሚጠበቅበትን ድርሻ እንዲወጣ እንደሚሰራ ገልጿል።በዚህ ላይ የምሁራን ሚና ጅማሮ ቀጣይነት እንዲኖረው ይደረጋልም ነው የተባለው። ምንጭ ፡-ኤፍ.ቢ.ሲ", "passage_id": "a17fa4782edafa47f40f5179aaa7dc7c" }, { "passage": "ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን ሁሴን ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት ወደ ስራ የተገባው  የተለጠጠ ዕቅድ ተይዞ ቢሆንም  ከተቀመጠው ግብ ጋር ተቀራራቢ ውጤት በመመዝገቡ ዜጎችን በየደረጃው ተጠቃሚ አድርጓል።የተመዘገበው ዕድገትም የአፍሪካ አህጉር አማካይ እድገት እጥፍ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፣ “ይህም ሌላው ዓለም ያልደረሰበትና ውጤታማ መሆኑን ያመለክታል”ብለዋል።ዕድገቱ ድህነትን በከፍተኛ ፍጥነት መቀነስ አስችሏል ያሉት አቶ ሬድዋን፣ የድህነት መጠኑ በ1997 ከነበረበት 39 በመቶ በተያዘው ዓመት መጨረሻ ወደ 22 በመቶ መውረዱንም በማሳያነት አቅርበዋል።በተጨማሪም “የዜጎችን ተጠቃሚነት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ አረጋግጧል፤ በአገር ደረጃ በምግብ ራሳችንን እንድንችልም አድርጎናል” ሲሉ ተናግረዋል።በአምስት ዓመታት ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ እንዲለማ የተደረገ ሲሆን፣ ግማሽ ያህሉ አርሶ አደርም ገበያ ተኮር የሆኑ ምርቶችን በሚያመርትበት ደረጃ ላይ ደርሷል።በቀጣዩ የአምስት ዓመት ዕቅድም እያንዳንዱ አርሶ አደር የመስኖ ተጠቃሚ እንዲሆንና በዓመት ሶስት ጊዜ እንዲያመርት ይደረጋል።የቁጠባ አቅምን ለማሳደግ የተያዘው ግብ ስኬታማ መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ ከዕቅድ ዘመኑ በፊት የነበረው የ43 ቢሊዮን ብር ቁጠባ ወደ 133 ቢሊዮን ብር ማደጉንም አመልክተዋል።ይሁን እንጂ ከሰሃራ በታች ካሉት የአፍሪካ አገሮች አማካይ የቁጠባ ምጣኔ ጋር ሲነጻጸር አሁንም በዝቅተኛ ደረጃ ላይ ስለሚገኝ ትኩረት ያሻዋል ብለዋል።አማካይ አገራዊ የዋጋ ግሽበቱን በነጠላ አኅዝ ማቆየት መቻሉ ሌላው በዕቅድ ዘመኑ የተመዘገበ ስኬት መሆኑንና በቀጣዩ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመንም መንግስት ይህንን ለማሰቀጠል እንደሚሰራ ተናግረዋል።በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ከተያዙት ግዙፍ ፕሮጀክቶች መካከል የስኳር ፋብሪካዎችና የአገር አቀፍ ባቡር ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜ አለመጠናቀቃቸውንም አንስተዋል።ለፕሮጀክቶቹ በጊዜያቸው አለመጠናቀቅም የፋይናንስ አቅም ውስንነትና የማሰፈፀም አቅም ጉድለቶች ዋነኛ ማነቆዎች እንደነበሩ ነው ሚኒስትሩ ያብራሩት።በአንጻሩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፣ የሲሚንቶና የብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ልማት ፕሮጀክቶች በታለመላቸው ጊዜ እየተከናወኑ መሆናቸውንም ሚኒስትሩ አስረድተዋል።በሁሉን አቀፍ የገጠር መንገዶች ተደራሽነት ፕሮግራም በዕቅድ ዘመኑ 71 ሺህ ኪሎሜትር መንገዶችን ለመገንባት የታቀደ ቢሆንም፤ ማከናወን የተቻለው 40 ሺህ ኪሎሜትር ብቻ በመሆኑ ሌላው የዕቅዱ ጉድለት ሆኖ ተነስቷል።በወጪ ንግድና በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ በኩል የተያዙት ግቦች በታለመላቸው መንገድ ሰኬታማ አለመሆናቸውም እንዲሁ።የቀጣዩ አምስት ዓመታት ዕቅድም በመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን የተመዘገቡ ስኬቶችንና የታዩ ጉደለቶችን በማገናዘብ የተዘጋጀ ነው። በጅምር ያሉትን ሥራዎችም ለመጨረስ ያስችላል ብለዋል ሚኒስትሩ።ስለሆነም በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ግብርናው በኢኮኖሚው ውስጥ ያለው የ40 በመቶ ድርሻ ወደ 36 በመቶ እንዲወርድ ይደረጋል፤ በምትኩ ኢንዱስትሪው በተለይም ደግሞ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ በኢንዱስትሪው ውስጥ የላቀ ድርሻ እንዲይዝ ይደረጋል።አቶ ሬድዋን እንዳሉት ይህንን ለማሳካት ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት አጠናክሮ ማስቀጠል፣ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ማነቆዎችን መፍታት በዕቅዱ ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች ናቸው።የአገር ውስጥ የቁጠባ አቅምን አሁን ካለው በበለጠ የማሳደግና የራሳችንን ልማት በራሳችን አቅም የማከናወን ሥራም በዕቅዱ ትኩረት ይሰጠዋል ነው ያሉት ሚኒስትሩ።የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታትና የልማታዊ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ አሰተሳሰብን በሁሉም አካባቢዎች ማስረጽ ሌላው ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ነው።እንዲሁም ስኬት በተመዘገበባቸው እንደ ትምህርት ባሉ የማህበራዊ ልማት መስኮችና በመሰረተ ልማት ዘርፉ ላይ ጥራትን ለማስጠበቅ እንደሚሰራ አቶ ሬድዋን ሁሴን ተናግረዋል።", "passage_id": "538d42b8b0617d12eb0f472682406cb7" }, { "passage": "በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ተንሰራፍቶ የቆየውን ችግር በቅጡ ለመረዳትና መፍትሔ ለመስጠት አዲሱ የግብርና ሚኒስትር ዶ/ር እያሱ አብረሃ፣ ኅዳር 16 ቀን 2009 ዓ.ም. በጠሩት ስብሰባ ባለሀብቶች ምሬታቸውን ገለጹ፡፡በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ካቢኔ ውስጥ ከተካተቱ አዳዲስ ሚኒስትሮች መካከል አንዱ የሆኑት ዶ/ር እያሱ፣ በበርካታ ችግሮች የተተበተበው የግብርና ኢንቨስትመንት ያለበትን ደረጃ ለማወቅና መፍትሔም ለማበጀት ይህንን ስብሰባ ቢጠሩም፣ አስቸኳይ ጉዳይ ገጥሟቸው ስብሰባውን አቋርጠው ሄደዋል፡፡በእሳቸው ምትክ ከአንድ ዓመት በፊት የተሾሙት የእርሻና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሰዓዳ ከድር ስብሰባውን መርተዋል፡፡በስብሰባው ላይ 100 የሚጠጉ ከፌዴራል መንግሥት መሬት የወሰዱ የግብርና ኢንቨስተሮች የተገኙ ሲሆን፣ የመናገር ዕድል የተሰጣቸው ኢንቨስተሮች በከፍተኛ ችግር ውስጥ የተዘፈቁ ቢሆኑም መፍትሔ የሚሰጥ አካል በመጥፋቱ ተስፋ የተጣለበት ዘርፍ እየመከነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ካሉት ችግሮች መካከል የመሬት አሰጣጥ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የመሠረተ ልማት፣ የብድር አቅርቦት ላይ ያሉ ችግሮች በዋነኛነት ይጠቀሳሉ፡፡በመሬት አሰጣጥ በኩል የፌዴራል መንግሥት ከክልሎች በውክልና የወሰደውን መሬት፣ የግብርና ኢንቨስትመንት መሬት አስተዳደር ኤጀንሲ ለባለሀብቶች ይሰጣል፣ ያስተዳድራልም፡፡ነገር ግን ኤጀንሲው በሰጠው መሬት ላይ ችግር ሲያጋጥም መፍትሔ እንዲሰጡ የሚጠበቁት ክልሎች ናቸው፡፡ ይህ አሠራር ለዘርፉ ማነቆ ሆኗል በማለት በስብሰባው ላይ ተነስቷል፡፡የመሬት አስተዳደር ኤጀንሲው በተለይ በጋምቤላ ክልል የሰጣቸው ቦታዎች መደራረብ የሚታይባቸው በመሆኑ ከፍተኛ ችግር አጋጥሟል፡፡ የግብርና ኢንቨስትመንት መሬት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አበራ ሙላት በዘርፉ ችግር እንዳለ አምነው፣ በተለይ በጋምቤላ ክልል በታችኛው መዋቅር የመልካም አስተዳደር ችግር መኖሩን ገልጸዋል፡፡ ለዘርፉም ብድር እየቀረበ አለመሆኑን አቶ አበራ ጠቅሰው፣ የብድር አቅርቦት ግን የእሳቸውን መሥሪያ ቤት እንደማይመለከት አስረድተዋል፡፡በስብሰባው ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ባለሀብቶች በመጀመሪያ ደረጃ ኤጀንሲው በትክክል የማያስተዳድረውን የእርሻ መሬት ለምን ይሰጣል? ኤጀንሲው በሰጠው መሬት ላይ ችግር ሲፈጠር ክልሎቹ እንዲፈቱት መጠበቅ አግባብ ነው ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች አቅርበዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪ ለግብርና ኢንቨስትመንት ብድር እንዳይቀርብ በደብዳቤ የጠየቀው መሬት አስተዳደር ኤጀንሲው ራሱ መሆኑን ባለሀብቶቹ ተናግረዋል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ብድር ቢያቆም እንኳ የእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፉ በመንግሥት ትኩረት የተሰጠው ዘርፍ እንደመሆኑ፣ የታገደው ብድር አሰጣጥ እንዲጀመር ማድረግስ አልነበረበትም ወይ?›› በማለት አንድ ባለሀብት ጠይቀዋል፡፡የጥጥ ኢንቨስትመንት የግብርና ሥራ ቢሆንም፣ የጥጥ ጉዳይን የሚከታተለው ዳይሬክቶሬት በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሥር በሚገኙ ተቋማት ውስጥ እንዲገባ መደረጉ አግባብ እንዳልሆነም ተገልጿል፡፡ከዚህ በተጨማሪም የኢንቨስትመንት አዋጁ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ባለሀብቶችን በመወከል የፋይናንስ አቅርቦት፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ የመሠረተ ልማት አውታሮች እንዲሟሉ ያደርጋል የሚል ቢሆንም፣ ኮሚሽኑ ይህንን አድርጎ እንደማያውቅ ባለሀብቶች በምሬት ተናግረዋል፡፡በደቡብ ኦሞ ኢንቨስት ለማድረግ ቦታ የወሰዱ ኢንቨስተሮችም ምሬታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለይ በደቡብ ኦሞ ለዓመታት መጠናቀቅ ያልቻለውና በአንድ ወቅት በመገንባት ላይ የነበረው የኦሞ ድልድይ በድጋሚ ችግር ውስጥ በመሆኑ፣ በጥልቀት ወደ እርሻ ሥራ መግባት አለመቻላቸውን ተናግረዋል፡፡በዚህ ሁኔታ እያሉ ግን የመሬት አስተዳደር ኤጀንሲው ማስጠንቀቂያ ከሰጣቸው ኩባንያዎች መካከል ኦሞ ቫሊ፣ ዳሰኒ እርሻ፣ ዶ/ር ጠአመ እርሻ፣ ዳሰነች እርሻ፣ ጉቲት እርሻ ልማት ይገኙበታል፡፡እነዚህ የእርሻ ልማት ድርጅቶች በራሳቸው ፋይናንስ በተወሰነ ደረጃ ሥራ እየሠሩ ቢሆንም፣ ድልድዩ ተጠናቆ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ብድር ሰጥቷቸው በስፋት ወደ ሥራ እንደሚገቡ ተስፋ ቢያደርጉም፣ ድልድዩ መጠናቀቅ ካለመቻሉም በላይ ተስፋ አስቆራጭ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ኤጀንሲው ችግሩን ከመፍታት ይልቅ ማስጠንቀቂያ መጻፉ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል፡፡የባለሀብቶቹን ቅሬታ የሰሙት ሚኒስትር ዴኤታዋ ወይዘሮ ሰዓዳ ችግሮቹን መረዳታቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት ለባለሀብቶቹ ዕገዛ ለማድረግ የሚያስችለውን ሥራ ለማከናወን እንደሚጥር ቃል ገብተዋል፡፡መንግሥት ጉዳዩን በጥልቀት እንደሚመለከተውና በአጭር ጊዜም መፍትሔ እንደሚሰጥ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "57d46e7302ea599540c27a0e159f546f" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ ሃምሌ 24/2005 (ዋኢማ) – አራተኛው የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡ የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን እንዳለውም የመድረኩ ዓላማ በኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢቨስትመንት ላይ በመወያየት ከዚያ የሚገኙ አዳዲስ ሃሳቦችን ለፖሊሲ አፍላቂዎች ግብዓት እንዲሆን ማድረግ ነው ።ኢትዮጵያን እንደ አውሮፓውያኑ የቀን አቆጣጠር በ2025 መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገራት ተርታ ለመሰለፍ በርካታ ስራዎችን እያከናወነች መሆኗ ይታወቃል።በዛሬው መድረክ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዲኤታው  አቶ ሲሳይ ገመቹ  እንዳመለከቱትም ፥ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ የኢንዱስትሪ መስኩን ማስፋፋትና የኢኮኖሚ መሪነቱን ከግብርናው ዘርፍ እንዲረከብ ማድረግ ዋናው ትኩረት ሊሆን ይግባል ።ኢትዮጵያ በርካታ ኢንዱስትሪዎችን ለመትከልና ኢኮኖሚያዊ እድገቷን ለማፋጠን ወደ ትግበራ የገባች ሲሆን ፥ አሁን ባለው ሁኔታም ዕቅዱን ማሳካት እንደሚቻል ነው ሚኒስትር ዲኤታው የተናገሩት።ይሁን እንጅ የአቅም ግንባታ ፣ የኢንዱሰትሪው ዘርፍን  ጠቀሜታ ለባለሃብቱ የማስተዋወቅ እና የመሰረት ልማት አቅርቦት  በበቂ ሁኔታ አለመከናወን ለዘርፉ ማነቆዎች መሆናቸውን ነው ያነሱት።ከዚህ አኳያም በዘርፉ የሚስተዋሉትን ችግሮች ለመቅረፍ በርካታ ስራዎች እየሰተሩ ስለመሆኑም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ዋና ስራ አስከያጅ አቶ ፍጹም አረጋ በበኩላቸው ፥ ካሁን ቀደም ባሉት አዋጆች ላይ ማሻሻያዎችን ለማድረግ መታቀዱን ነው የሚገልፁት።እነዚህ በአዱስትሪው መስክ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሃገራት በመነሳት የተዘጋጁት መመሪያዎች የሚፀድቁ ከሆነም ፥  የውጭ ቀጥታ አንቨስትመንትን ከመሳብ አንፃር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸውም ነው አቶ ፍፁም የሚናገሩት ሲል ፋና ዘግቧል።በጃፓን የፖሊሲ አማካሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ኪንቼ ኦህኖ ደግሞ ፥ ኢትዮጵያ ወደ አንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋጋር የሚያበቃ እምቅ አቅም አላት ይላሉ።ለውጭና ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች የሚመች ፖሊሲ ፣ በቀላል ዋጋ የሚገኝ የሰው ሃይልና ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ መስክ ላይ እየሰለጠነ ያለ የተማረ የሰው ሃይል ዋናዎቹ ሲሆኑ ፥ በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ ሁሉንም ማሟላት እንደምትችል ገልጸዋል።", "passage_id": "f940c0f4aea73b3666c3e6e15ef4ea77" }, { "passage": "በሀገራችን የግብርና ሥራ የረጅም ዘመናት እድሜ ቢኖረውምና አብዛኛው ህዝባችን በዚሁ የሚተዳደር ቢሆንም የእድሜውን ያህል አድጎና ዘምኖ ዜጎችን በሚጠበቀው መጠን ተጠቃሚ እያደረጋቸው ነው ለማለት የሚያስደፍር አይደለም። ዛሬም ዘርፉ እጅግ ኋላቀር ከመሆኑ አንጻር ሀገሪቱ ሰፊ የሚለማ መሬት እያላት የምግብ እህል ከውጭ በማስገባት ላይ ትገኛለች ።ለዚህም በሚሊዮኖች የሚቆጠር የውጭ ምንዛሪ ታወጣለች። \nበአንድ በኩል የግብርና ሥራው በዝናብ ውሀ ላይ ጥገኛ ሆኑ መቆየቱ ፤በሌላ በኩል ደግሞ አሁንም የግብርናው ዘርፍ በሚፈለገው ደረጃ በዘመናዊ ትክኖሎጂ መታገዝ አለመቻሉ ፤ በዘርፉ የተሰማራው አብዛኛው የሀገሪቱ ህዝብ ሕይወት በተጨባጭ መለወጥ አልተቻለም ። \nመንግሥት በዘርፉ ያለውን ችግር በመፍታት ምርታማነቱን ለማሳደግ ባለፉት ዓመታት ሰፊ ሥራዎችን በመስራት ብዙ ጥረቶችን ቢያደርግም ፤ የተገኘው ውጤት ግን የታሰበውን ያህል አልነበረም፤ አልሆነምም።እንዲያውም ሀገሪቱን ለከፋ ብክነት ዳርጓታል:: \nሰፋፊ መካናይዝድ እርሻዎችን ለማስፋፋት ተብሎ የተደረጉ ጥረቶች ከመሬት ወረራና ካልተገባ የብንክ ብድር ባለፈ ያመጡት ተጨባጭ ለውጥ የለም ፤የእርሻ ግብአት ማምረቻ ፋብሪካዎችን /የማዳበሪያ ፋብሪካ / ለመገንባት የተደረገውም ሙከራ በቢሊዮን የሚቆጠር የሐገር ሀብት ለብክነት ከመዳረግ ባለፈ ያመጣው አዲስ ነገር የለም ። \nበዘርፉ ባለው የተደራረበ ችግር የተነሳም ዛሬም ሀገሪቱ ራሷን መመገብ የምትችልበት ደረጃ ላይ አልደረሰችም። ዛሬም ከፍተኛ መጠን ያለው የእርሻ መሬት ጾሙን ያድራል ወይም ደግሞ የክረምት ወራትን በመጠበቅ ማምረት የሚችለውን ያህል ማምረት ሳይችል ቆይ ቷል። \nይህ እውነታ ባልተቀየረበት ሁኔታ ዛሬ ደግሞ የኮሮና ቨይረስ በሀገሪቱ ገብቶ ነገሩን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አድርጎታል። የቫይረሱ ስርጭት ከፈጠረው ስጋት ጋር በተያያዘ አደጋ ውስጥ ከወደቁት ዘርፎች አንዱ የእርሻ ሥራው ነው። \nስጋቱን ደግሞ የከፋ የሚያደርገው የበሽታው ወረርሽኝ የተከሰተበት ወቅት ትልቁ የግብርና ሥራ የሚሰራበት ወቅት ላይ መሆኑ ነው። ወቅቱ ለሀገሪቱ የምግብ እህል ምርት ወሳኝ የዝግጅት ወቅት ነው። ይህንን የዝግጅት ወቅት በአግባቡ ካልተጠቀምንበት ድንገትም ሀገሪቱ በሌላ ስጋት /የረሀብ ስጋት/ውስጥ ማለፏዋ የግድ ይሆናል። \nይህንንም ተከትሎ መንግስት የእርሻ ሥራው በኮረና ቫይረስ ወረርሽኙ ስጋት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። የእርሻ ሥራው ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረግ ጀምሮ ለእርሻ ሥራው የሚያስፈለጉ ግብአቶች ቀድሞ ወደሀገር ውስጥ ከማስገባት ጀምሮ ለአርሶ አደሩ በወቅቱ እንዲደርሱ እያደረገ ያለው ጥረትና እየተመዘገበ ያለው ወጤት የሚበረታታ ነው። \nከዚህም በላይ መንግሥት የግብርና ሥራውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ስጋት እንዳይሸፍነው የቫይረሱን መከላከል ሥራ ግብርናውን ከማስቀጠል ጋር አቀናጅቶ እየሰራ መሆኑ ዛሬንና ከዛሬ በኋላ ያሉትን ቀናት ተሳቢ አድርጎ የሚከናወን በመሆኑ፤ ከአንድ የአደጋ ስጋት ወደ ሌላ የአደጋ ስጋት ሊደረግ ይችል የነበረውን ጉዞ ማስቀረት የሚያስችል ይሆናል። \nይህ የሚሆነው ግን በግብርናው ዘርፍ ያሉ አካላት በሙሉ የጉዳዩን አሳሳቢነት ተረድተው ሰፊ ርብርብ ሲያደርጉ ብቻ ነው። ይህን ለማድረግ ደግሞ የኮረና ቫይረስ ከጤና ችግር ባለፈ በግብርናው ላይ ሊያስከትል የሚችለው አደጋ የከፋ መሆኑን በአግባቡ መረዳትን ይጠይቃል። \nበኛ አገር የኮሮና ቫይረስ ሊያስከትል የሚችለው የጤና አደጋም ሆነ በግብርናው ዘርፍ ሊያስከትል የሚችለው አደጋ በመተንፈሻ አካል ችግር የሚፈጠር ሞትና በረሀብ ምክንያት የሚፈጠር ተመሳሳይ ሞት ነው:: ይሄኛው ሞት ከዚህኛው ሞት ይሻላል የሚል የሞት ምርጫ ባይኖርም ምርጫ መሆን የሚገባው ሞትን ማስቀረት መሆን አለበት። \nከዚህ አንጻር በአሁኑ ወቅት ለግብርናው ሥራ በአንድ በኩል ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ ከግምት ውስጥ በማስገባት መንግሥት እየሰራ ያለው ሥራ የሚበረታታና የሁሉንም ቀና ትብብር የሚፈልግ ነው። ከትብብር በላይም የአደጋ ጊዜ የዜግነት ኃላፊነት ጭምር ነው። \nወቅቱ ለሀገርና ለህዝባችን ስጋት የሆኑ ሁለት የአደጋ ምንጭ ተግዳሮቶችን በተቀናጀና ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ አሸንፎ ለመውጣትና ነገን በተሻለ መልኩ መጠበቅ የሚያስችል ተስፋን በመሰነቅ የብልጽግና ጉዟችን ላይ ያጋጠሙንን እነዚህን ተግዳሮቶች መደመልካም አጋጣሚ የመለወጥ ማስተዋልና ጥበብ የሚጠይቅ ነው። ለዚህ ደግሞ እራሳችንን በተገቢው መልኩ ልናዘጋጅ ይገባል! \nአዲስ ዘመን ሚያዝያ 20/2012", "passage_id": "1073b31194320b529504c1bded0c8301" } ]