input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ላለፉት ሶስት ዓመታትም በአንድ መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት ዉስጥ በማህበራዊ አገልግሎት ሰራተኝነትና በሥነ ልቡና አማካሪነት ተቀጥራ እየሰራች ትገኛለች።
|
ቤዛዊት የክበቡን ዓላማ በመደገፍ አባል የሆነችዉ ከ ወር በፊት ሲሆን አባላቱን የተዋወቀቻቸዉም በፌስ ቡክ ነዉ።
|
ወጣቶቹ ለበጎ አድራጎት ስራዎቻቸዉ ጫማ በመጥረግ የሥነ ፅሁፍ ምሽቶችን በማዘጋጀት እና ከበጎ አድራጊ ግለሰቦች የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፎችን በመቀበል ይሰራሉ።
|
እዛ ላይ ያሉ ቃላቶች ናቸው ችግር እየፈተጠሩ ያሉት ።
|
እና አብዛኛው ሰው ትንታኔ ይሰጣል ለነገሩ ክብደት ሰጥቶ አይደለም ።
|
ከዚያ ነው ወደ መሬት ወርዶ ብዙ ዩኒቨርሲቲዎች ብዙ ቦታዎች እና ከተማዎች እየተበጠበጡ ያሉት።
|
ካለች በኋላ ወጣቱን ይህንን ለመለወጥና ለማስተካከል እንችላለን የሚል እምነት አለኝ።
|
በእነዚህ ዉይይቶች ፌስ ቡክ ላይ ያለዉ ገፅታ ከነባራዊዉ ሁኔታ የተለዬ መሆኑን ተገንዝበናል ይላል ወጣት ናኦል።
|
የክበቡ አባላት በአዳራሽ ከሚያዘጋጁት ዉይይት በተጨማሪ ዘረኝነትን የሚቃወም ፍቅርና ሰላምን የሚሰብኩ ቃላትን በመጠቀምና በተናጠል ሰዎችን በማነጋጋርም የጎዳና ላይ ቅስቀሳዎችንም ያደርጋሉ።
|
የዚህ አይነቱ ቅስቀሳ በኢትዮጵያ ብዙ የተለመደ ባይሆንም ከማህበረሰቡ ያገኙት ምላሽ ግን በጣም ጥሩ እንደነበር ወጣት ገላዉዲዎስ ያብራራል።
|
እንደ ወጣት ገላዉዲዮስ እምነት እስካሁን ለወጣቶች መፍትሄ የሚፈልጉት ትልልቆቹ በመሆናቸዉ ወጣቱ የመፍትሄ አካል አልነበረም።
|
በመሆኑም ወጣቶች በሚያመቻቸዉ መንገድ በመሰባሰብና በመወያየት የሀገሪቱን ችግር በመፍታት ሂደት ሊሳተፉ ይገባልም ይላል።
|
ወጣቶች በያሉበት በጣም ብዙ ችግር ያለበት አገር ስለሆንን ትንሽ ነገር ማድረግ እንኳ በጣም የ ሶሉሽን አካል እንደ መሆን ነዉ።
|
ከክፉ ስራ ጋር አላለመተባበር ራሱ ትልቅ የ ሶሉሽን አካል መሆን ነዉ።
|
ወጣቶቹ በግል በመሰረቱት ክበብ በትርፍ ጊዜያቸዉ የሚንቀሳቀሱ በመሆኑ የሚሰጡት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በአቅምም በጊዜም የተወሰነ በመሆኑ የፈለጉትን ያህል አለመስራታቸዉን ይገልፃሉ።
|
በመሆኑም በቀጣይ በተሻሻለዉ የሲቪክ ማህበራት እና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች አዋጅ መሰረት ክበቡን ህጋዊ ሰዉነት ለማሰጠት አቅደዋል።
|
ይህም በቦታና በጊዜ እንዲሁም በአቅም ሳይወሰኑ ሀገራቸዉን በበጎ ፈቃድ ለማገልገል እንደዚሁም ሰፊ ስራ ለመስራት እንደሚያስችላቸው ይናገራሉ።
|
ኢትዮጵያ በ ኛዉ የተመድ ጉባኤ የኢትዮጵያ ተሳትፎና የሕዳሴዉ ግድብ ኢትዮጵያ በ ኛው የተመድ ጉባዔ በከፍተኛ ባለሥልጣናት ደረጃ እንደምትሳተፍ ተገለጸ።
|
ኢትዮጵያ በተመድ ኛ ጉባዔ በከፍተኛ ደረጃ ትሳተፋለች ኢትዮጵያ በ ኛው የተመድ ጉባዔ በከፍተኛ ባለሥልጣናት ደረጃ እንደምትሳተፍ ተገለጸ።
|
አገሪቱን የሚያስተዳድረው ወታደራዊ ምክር ቤት ሥልጣኑን ለሲቪል መንግሥት እንዲያስረክብ የሚሹት የአገሪቱ ተቃዋሚዎች መከፋፈል ቀውሱ እንዲህ በቀላል መፍትሔ ለምግኘቱ አጠራጣሪ አድርጎታል።
|
የሱዳን የቀድሞ ፕሬዝዳን ኦማር ሐሰን አል በሽር ከስልጣን ገለል ቢሉም ይመሩት የነበረው ሥርዓት አሁንም እንዳለ ነው።
|
የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች የአፍሪካ ኅብረት እና ኢትዮጵያን ጨምሮ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በየራሳቸው መንገድ ለሱዳን ፖለቲካዊ ቀውስ መፍትሔ እያፈላለጉ ነው።
|
በሱዳን የሚኖር የኃይል አሰላለፍ ለውጥ በኢትዮጵያ እና የምስራቅ አፍሪካ አገራት ላይ ምን አይነት ተፅዕኖ ያሳድራል
|
በዛሬው የማኅደረ ዜና መሰናዶ ገበያው ንጉሴ የሚመለከተው ጉዳይ ነው።
|
ኮሮና በአውሮጳ ያሳደረው ተጽእኖ በአሜሪካ እና በአውሮጳ ተህዋሲው በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተሰራጨ ነው።
|
ዶ ር እንዳወቀ የጠፈር ሳይንስ በአዳጊ አገራት በማስፋፋት ይታወቃሉ ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ተግባር ላይ የዋለው የማስተማሪያ ዘዴ የአንደኛ ክፍል ተማሪዎች በፊት አባጫዳ በሚል ሲማሩ የነበሩበትን የአፋን ኦሮሞን ፊደል አሁን ላአጋማ በሚል ተክቷል።
|
ን በመዋዕለ ሕፃናት ተምረው ወደ አንደኛ ክፍል የገቡት ተማሪዎች በአዲሱ የማስተማሪያ ዘዴ እንደተደናገሩና ይህም ለአስተማሪዎችም ይህም ትልቅ ችግር መሆኑ ተገልጿል።
|
ይህ ጉዳይ በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ከተሰራጨ በኋላ በሁለተ ጎራዎች የተከፈለ ከፍተኛ ክርክር ቀስቅሷል።
|
የመጀመሪያው ቡድን በትዊተር ላይ የተሰኘና የሚል ሃሽታግ በመጠቀም የፊደሉ ቅደም ተከተል እንዳይቀየር ዘመቻ አካሂደዋል።
|
የተባባሩት መንግስት እቅድ በሆነው የምዕተ አመቱ የልማት ግቦች ዉስጥ ድህነት ቅነሳ አንዱ ነዉ።
|
አገሮች በ ዘዴ በመጠቀም በ ቋንቋዎች ላይ የተማሪዎች የማንበብና የመጻፍ ችሎታ መፈተሻቸውን ዶክተር ቶላ ባርሶ ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል።
|
በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተወስደው ሺህ ተማሪዎች ላይ ጥናቱ ተደርጓል።
|
በኦሮሚያም በ ዞን ዉስጥ በ ትምህርት ቤቶች ላይ ጥናቱ ተካሂዷል።
|
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአፋን ኦሮሞ ክፍለ ትምህርት የስነ ቋንቋ መምህር የሆኑት ዶክተር ቶላማርያም ፉፋ በዝህ ጥናት ላይ መሳተፋቸዉን ይናገራሉ።
|
እንደ ዶክተር ቶላማርያም ገለጻ በቋንቋዎች ዉስጥ የትኛዉ ፊደል ተደጋግሞ እንደሚመጣ ወይም የሚለካ ፕርምያር ፕሮ የተሰኘዉን ሶፍትዌር ተጠቅመዋል።
|
በዝህም መሰረት የተገኘዉ ዉጤት ለምሳሌ በአፋን ኦሮሞ ፍደል ዉስጥ ከ በላይ ተደጋግሞ መጥቷል።
|
ተደጋግመው በመጡት ፊደላት ላይ በመመርኮዝ ለአንደኛ ክፍል አዲስ መፅሃፍ መዘጋጀቱንም ይናገራሉ።
|
በመጻፉም ላይ ተማሪዎች በፊት በሚመሩበት ፈንታ በ እንዲማሩ መደረጋቸዉን ዶክተር ቶላማርያም አክለውበታል።
|
ይልቁንስ በፊደል ተርታ ላይ በ ኛ ደረጃ ላይ እንደተቀመጠጠቅሰዋል።
|
የዚህ ፕሮጄክት አባል የሆኑት የስነ ቋንቋ ባለሙያ አቶ አማኑኤል ራጋ ይህ ዘዴ አለው ያሉትን ተጽዕኖ ለዶይቼ ቬሌ እንዲህ ገልጸዋል፥
|
ሁለተኛዉ የዚህ የአዲሱ የቁቤ አፋን ኦሮሞ ታኣማኒነት ጥያቄ ዉስጥ ነዉ ያለዉ።
|
እዉነት ይህ የቁቤ ችግር ነዉ ወይ የሚል ጥያቄ ማንሳት አለብን።
|
ከዛ በተረፈ የቁቤ አፋን ኦሮሞ ከኦሮሞ ቀንቋ ታሪክና ከሕዝቡ ጋር የተገናኘ ነዉ።
|
የአሮሞ ማንነት በዚህ ሰዓት የሚገለጸዉ ወይም ኦሮሞነትን ለመግለጽ የቀረዉ ነገር ካለ ቀንቋዉ ነዉ።
|
ስለዚህ ይህን ከማንነት ጋር የተቆራኘ ነገር መነካካት አስፈላጊ አይደለም።
|
ተማሪዎችን መጀመርያ የሚለዉን እስከ መጨረሻ ድረስ ካስተማርክ በኋላ የማንበብና መጻፍ ማስተማርያ ዘዴ ነዉ የተባለዉን ብታስከትል ኖሮ ችግር አልነበረም።
|
ከ የሚጀምረዉን ፍደል ሰዉ በመጽሀፉ ሲመልከት የቁቤ አፋን ኦሮሞ ቅደም ተከተል ተቀየረ የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሱና መከራከሩ ትክክል ነበረ።
|
ባለሙያዎችን ለምን ቀየራችሁት ተብለው ሲጠየቁም በመዋለ ሕፃናት የተለመደዉን ፊደል ተምረው ስለሚመጡ የሚል መልስ ተሰጥቶ ነበር።
|
ከከተማ ዉጭ በገጠር ያለዉ አብዛኛዉ ተማሪ መዋዕለ ሕፃናት ስለሌለ የተለመደዉን ፊደል የት ተምረው ይመጣሉ ብዬ ጠይቃቸዉ ነበር።
|
ጽህፈት ቤቱ ህብረተሰቡንና አብዣኞቹን ባለሙያዎች ስለማስተማሩ ዘዴ አለማሳወቁን ዶክተር ቶላ እንደ ችግር ይቀበላሉ።
|
በጥናቱ እና መጽሀፉን በማሳተም አስተዋፅዖ የነበራቸዉ ዶክተር ቶላማርያም ዶክተር ቶላ ያቀረቡትን ሃሳብ ይጋራሉ።
|
ባላፈዉ እሁድ የክልሉ ትምህርት ጽህፈት ቤት ብሮ ባለሙያዎችን በመሰብሰብ በአንድ ወር ዉስጥ መጻሃፉ እንዲገመገም የጎደለዉ እንዲሟላ ማመወያየቱን ለመረዳት ተችለዋል።
|
የስነ ቋንቋ ባለሙያዉ አቶ አማኑኤል ራጋ ትምህርት ጽህፈት ቤቱ ሊያደርግ ያቀደዉን ለዉጥ ተቀብለው ዉጤቱን ግን ቆይቶ የሚታይ ይሆናል ብለዋል።
|
እንደ ጎርጎሮሳዊው የተመሠረተው የሃገራቱ ቡድን ቦርኪናፋሶ ማሊ ሞሪታንያ ኒጀር እና ቻድን ያቅፋል፡፡
|
የአውሮጳ ኅብረት መቀመጫ በሆነችው ብራስልስ የሚገኘው ዘጋቢያችን ኅብረቱ ለመርሃ ግብሩ ማስፈጸሚያ ስለለገሰው እርዳታ ዘገባ ልኮልናል፡፡
|
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ንግድ ባንክ ሀብታሙን እንጅ ድሃውን አማራ አልፈልገውም በማለቱ በርካቶች አማራጭ ባንክ እየፈለጉ ነው።
|
ገንዘቡን ከንግድ ባንክ በማውጣት ደግሞ ይበልጥ አጋርነቱን ማሳየት አለበት ሲል በንግድ ባንክ ላይ የተነሳውን ተቃውሞ አበረታቷል።
|
ጌታቸው በተቃውሞ የተቀዳደዱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መገልገያ ደብተሮች የሚያሳይ ምስል በፌስቡክ ገጹ አሰራጭቷል።
|
ኪዳነማርያም ደግሞ ንግድ ባንክ ላይ የተከፈተው ዘመቻ አግባብነት የለውም።
|
ንግድ ባንክ መስጠት ካልፈለገ ትዝብቱን ለህዝብ እንተወው የሚል ሐሳባቸውን አጋርተዋል።
|
ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ቀጥሎ የሐገሪቱ እና የኢትዮጵያውያን ሐብት ነው በማለት ዘመቻውን ነቅፈዋል።
|
በማኅበራዊ ድረ ገፆች የተደረገው ዘመቻ ፍሬ አፍርቶ ባንኩ ሚሊዮን ብር ለመስጠት ቃል መግባቱን የሚጠቁም ደብዳቤ ተሰራጭቶ ነበር።
|
ወሬው ከተሰማ በኋላ ደጀን ምንይሉ ንግድ ባንክ ሚሊዮን ብር እያለቃቀሰ ሰጠ ነዉ ምትሉኝ
|
በገዛ ገንዘባችንም አንደለልም ከዚህ በኋላ ለሁሉም ጉዳይ የራሳችን ምርጫዎች ይኖሩናል ሲሉ ሐሳባቸውን አጋርተዋል።
|
ባንኩ ለአምቦ ስታዲየምም ሆነ ለአማራ ክልል ተፈናቃዮች የሰጠው የገንዘብ ድጋፍ የለም።
|
ስለሆነም እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ የሚያገለግለውና የሚደግፈው ፍትሃዊና ምክንያታዊ በሆነ አግባብ በራሱ ተነሳሽነት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል የሚል ሐሳብ ይዟል።
|
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለተፈናቃዮች ድጋፍ አልሰጠም የሚለው ዘመቻ የቀሰቀሰው ፍጭት ከፍ ብሎ የተቋሙን አመራሮች የብሔር ስብጥር ወደማጠያየቅ ተሻግሯል።
|
የማኅበራዊ ድረ ገፆች ተጠቃሚዎች አራማጆች እና ፖለቲከኞች ይኸንንው የብሔር ስብጥር ያሳያል ያሉትን ቁጥር እያጋሩ ነው።
|
ቆጠራው የኢትዮጵያ መንግሥት በመጪው መጋቢት ቀን ይጀመራል ተብሎ ይጠበቅ የነበረውን የሕዝብ እና የቤት ቆጠራ ለማራዘም ሐሳብ አቅርቧል።
|
ዮሐንስ የተባሉ የትዊተር ተጠቃሚ የኢትዮጵያ የሕዝብ ቆጠራ ውጤትን ሳስበው ሳስበው በጣም ያስቀኛል።
|
ኦሮሞ እና አማራ እያንዳንዳቸው ሚሊየን ነን ማለታቸው አይቀርም ሲሉ በቀልድ ሥራው የገጠመውን ፈተና አስቀድመው ለመጠቆም ሞክረው ነበር።
|
የማራዘም ሐሳቡ በይፋ መቅረቡ ከመሰማቱ በፊት ማሒ የተባሉ ትዊተር ተጠቃሚ የሕዝብ እና የቤት ቆጠራውን እናራዝመው።
|
በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ቆጠራውን ለማካሔድ ትክክለኛው ጊዜ አይደለም።
|
ኖሌ ጃላል የተባሉ የትዊተር ተጠቃሚ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከቆጠራው አውጪኝ።
|
ኖሌ ለመሆኑ ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን በቆጠራው እንዴት ሊያካትቷቸው አቅደዋል
|
በተለያዩ ግጭቶች የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ መኖሪያ ቀያቸው አለመመለሳቸው ቆጠራውን ለማራዘም ካስገደዱ ምክንያቶች መካከል እንደሚገኝበት የጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
|
ዐቢይ ኢትዮጵያውያን አቅማቸውን በማኅበራዊ ሚዲያ ዐውደ ውጊያ ሀገር ለማተራመስ ከመጠቀም እንዲቆጠቡ መክረዋል።
|
አለሙ ማንአለብህ አንዳንድ ጊዜ ጠቅላይ ምኒስትሩ እንደ አራማጅ ይሆናሉ።
|
ትክክል የሚሰሩ እውቅና ሊሰጣቸው የተሳሳተ ሥራ የሚሰሩ ደግሞ በሕግ ሊጠየቁ ይገባል የሚል አስተያየታቸውን በጠቅላይ ምኒስትሩ ደብዳቤ ግርጌ አስፍረዋል።
|
ጴጥሮስ ታደሰ በበኩላቸው ያለውን እውነት ማወቅ አለበኝ ብዬ ሙሉ ፅሁፍን አነበብኩት።
|
እውነት አለህ በፍቅር ታምናለህ እውነቱን ለህዝብ አስረዳ ውስጣችሁ ምንድን ነው የገባው
|
ቆፍጠን መረር ጨከን ማለት ካልቻሉ ሀገራችን እንዳይሆን እየሆነች ነው።
|
ከሙሉ አክብሮት ጋር ቦታዎን ለሚመጥነን ጉልቤ መሪ ይልቀቁና የመኖርም የመሥራትም ዋሥትናችን ይረጋገጥ የሚል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
|
ጃራ ፈጠነ በበኩላቸው የተከበሩ ጠቅላይ ምኒስትር የማኅበራዊ ድረ ገፆች አጠቃቀምን የሚገዛ መመሪያ ይዘጋጅ ዘንድ ያስቡበት።
|
ፅንፈኞች ኹከት ከመፍጠራቸው በፊት ጊዜ ያለ አይመስለኝም ሲሉ ሥጋታቸውን ገልጸዋል።
|
ጌታቸው ሳሙኤል ፈለቀ በወገናቸው እነዚህ የሀሰት ዜና የሚፈበርኩትን ለይቶ እርምጃ የማይወሰደው ለምንድ ነው
|
ያም ከሆነ ሶሻል ሚዲያውን ድርግም አርጎ ሰው ልቡን እስኪገዛ መዝጋት ነው ሲሉ ከጃራ ፈጠነ ጋር ተመሳሳይ ሐሳብ አንጸባርቀዋል።
|
ኢትዮጵያ ድሬደዋ አዲስ ከንቲባ ተሾመላት የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት በዛሬው ዕለት አዲስ ምክትል ከንቲባ ሾመ።
|
በፊደራል መንግሥት እና በአስሰተዳደሩ የተከናወነው የፖለቲካ ሪፎርም አካል ተደርጎ የሚወሰድ ነው የዛሬው የአመራር ለውጥና ሽግሽግ።
|
በዚህ ሂደት በዛሬው ዕለት በምክትል ከንቲባነት አስተዳደሩን እንዲመሩ የተሾሙት አቶ መሀዲ ጌሬ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት እንደሚሰሩ ተናግረዋል ፡፡
|
ምክትል ከንቲባው የወጣቶችን ችግሮችን ለመፍታት ከወጣቱ ጋር በሰለጠነ አግባብ እንሰራለን ብለዋል ፡፡
|
በዕለቱ የም ቤቱ ስብሰባ በሀላፊነት የተሾሙ አካለት ሀላፊነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን በቃለ መሀላ አረጋግጠዋል ፡፡
|
በአስተዳደሩ የተካሄደው የፖለቲካ ሪፎርም በሚፈለገው መልኩ ውጤት ስለማምጣቱ ቀጣዩ ጊዜ ምላሽ ይሰጣል።
|
ወባ መሰሉ ዴንጊ በሽታ በኢትዮጵያም መስፋፋት ጀምሯል በመላው ዓለም በበርካታ ሀገራት በስፋት የሚታየው የዴንጊ ትኩሳት በኢትዮጵያ እምብዛም ስሙ ሲነሳ አይሰማም።
|
በቅርቡ የተደረገ ጥናት ግን በሽታው በሰሜን ኢትዮጵያ ባሉት በመተማ እና ሁመራ መታየቱን አመልክቷል።
|
በአካባቢው በሽታውን እንደ ወባ የመውሰድ ችግር እንዳለ ጥናቱን በዋነኛነት ያካሄዱት የጎንደር ዩኒቨርስቲ ምሁር ይናገራሉ።
|
በርካቶችን ለአልጋ በሚዳርግባቸው በእስያ ደቡብ አሜሪካ እና ምዕራብ ፓስፊክ ባሉ ሀገራት በከፍተኛ የጤና ችግርነት ተመዝግቧል።
|
በመላው ዓለም ደግሞ በዓመት እስከ ሚሊዮን ሰዎች በበሽታው እንደሚለከፉ በጉዳዩ ላይ የተደረገ አንድ ጥናት ጠቁሟል።
|
በበሽታው ተጋላጭነት ላይ የተደረገ ሌላ ጥናት ቁጥሩን ከሚሊዮን ወደ ቢሊዮን ያሻግረዋል።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.