input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
እንደ ጥናቱ ከሆነ በ ሀገራት ለበሽታው የመጋለጥ አደጋ የተደቀነበት ህዝብ ቢሊዮን ይሆናል።
|
ከዓለም ህዝብ ግማሽ ያህሉን ሊያጠቃ ይችላል የሚባልለት ይህ በሽታ ዴንጊ ፌቨር ይባላል።
|
በጎንደር ዩኒቨርስቲ በሜዲካል ማይክሮ ባዮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት አቶ ጌታቸው ፈረደ ስለበሽታው ምንነት ያስረዳሉ።
|
ትኩሳት በዋናነት ሆኖ ማንቀጥቀጥ የመገጣጠሚያ ቦታዎች ህመም ማቅለሽለሽ ይኖራል ።
|
እነዚህ ደግሞ በወባም በሌሎችም በሽታዎች የሚታዩትን ነው እርሱም የሚያሳየው እና ብዙም በምልክት መለየት ከባድ ነው አይቻልም።
|
ከሦስት ዓመት በፊት በተደረገ ጥናት ይህ ቁጥር በሦስት እጥፍ ጨምሮ ተገኝቷል።
|
የዓለም ጤና ድርጅትን የመሳሰሉ ተቋማትን እያሳሳባቸው ያለው የቁጥሩ እንዲህ በፍጥነት መመደንግ ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም በሽታው ወዳልታየባቸው ሀገራት መስፋፋቱ ነው።
|
ከዓመታት በፊት በሽታው አይደለም በኢትዮጵያ በአፍሪካ ደረጃም ይሄን ያህል የሚወራለት አልነበረም።
|
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በሽታው በአህጉሪቱ እዚህም እዚያም ይታይ ይዟል።
|
የዛሬ ሁለት ዓመት በቡርኪናፋሶ በተቀሰቀሰ የዴንጊ ወረርሽኝ ከአንድ ሺህ የሚልቁ ሰዎች በበሽታው ተጠቅተዋል ተብሏል።
|
በኢትዮጵያም በተመሳሳይ ወቅት በድሬዳዋ እና ሶማሌ ክልል ወረርሽኞች መከሰታቸውን የናሙና ምርመራ ውጤቶች አመላክተዋል።
|
እኔ እንዳየሁት ወረርሽኝ ተነስቶ በጣም ከፍተኛ ትኩሳት ያለባቸው በሽተኞችን ሪፖርት ተደረጉ።
|
ሪፖርት ሲደረግ እዚያ ከድሬዳዋ ላይ ምክንያታቸው ያልታወቁ ግን ብዙ በሽተኞች ታመዋል።
|
ወባን ጨምሮ ታይፎይድ የሎው ፊቨር አይነት ብዙ በሽታዎችን መርምረዋል።
|
ያ ነው እንግዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ሪፖርት የተደረገው ሲሉ የጥናቱን ውጤት ያስታውሳሉ።
|
የጎንደር ዩኒቨርስቲው መምህር በሌሎች በሽታዎችን ላይ ከባልደረቦቻቸው ጋር ጥናቶች ባደረጉባቸው የመተማ እና ሁመራ አካባቢዎችም ተመሳሳዩን አስተውለዋል።
|
ወባም ከሌለ ከዚህ በፊት ካደረግነው ጥናት እዚያ አካባቢ በብዛት የሚገኙት እንደ ካላዛርም ከሌላቸው ከዚህ ተነስተን ምን ሊሆን ይችላል
|
የእነ አቶ ጌታቸው ጥናት ውጤት እንደሚያመለክተው በመተማ ከተመረመሩት ናሙናዎች መካከል አርባ በመቶው የዴንጊ ፊቨር ተገኝቶባቸዋል።
|
ዘጠኝ አጥኚዎች የተሳተፉበት ይህ ጥናት በግንቦት ዓ ም በሳይንስ መጽሔቶች ጆርናሎች ላይ ታትሟል።
|
አጥኚዎቹ ጥናቱን በሚያካሂዱበት ወቅት ካስተዋሉት ነገር አንዱ ዴንጊ ፊቨር በበሽታነት እንኳ ያለመታወቁ እውነታ ነው።
|
አካባቢው ላይ ቃለ መጠየቅ ስናደርግ ዴንጊ ምናምን ስንል ሙያተኞቹ ጭምር ምንድነው ይሄ በሽታ ሲሉ ነበር።
|
እና ሙሉ ለሙሉ እንደዚህ አይነት የለም ተብሎ ነበር የሚታወቀው ሲሉ በአካባቢው የተመለከቱትን ያጋራሉ።
|
የእስያ እና የደቡብ አሜሪካ በሽታ ይባል የነበረው ዴንጊ ፊቨር በአፍሪካ ሊያውም በኢትዮጵያ እንዴት ሊገኝ ቻለ
|
በሚል የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ምክንያቱን በትክክል ለማወቅ ተጨማሪ ዝርዝር ጥናቶች ያስፈልጋል የሚል ምላሽ ይሰጣሉ።
|
በሽታው በጎረቤት ሀገራት ጭምር እንደታየ የሚናገሩት ጥናት አድራጊው ምክንያቶች ሊሆኑ ይችላሉ ያሏቸውን ያስቀምጣሉ።
|
በአሁኑ ጊዜ ከአየር ንብረት ለውጥ እና ከከተሞች መስፋፋት ጋር ተያይዞ እንደ ወባ ትንኝ አይነት የበሽታ አምጪ ተዋህሲያን በቀላሉ እንዲራቡ ያደርጋል።
|
ለምሳሌ በአሁኑ ጊዜ ያው በኢትዮጵያ ውስጥ ከተሞቹ እየተስፋፉ ነው።
|
ከእነኚህ መስፋፋት ጋር ተያያዞ በቀላሉ እርጥበት ውሃ የመሳሰሉ ለወባ ትንኞች መራቢያ ምቹ ነገሮች ይፈጥራል።
|
እነኚህ ዴንጊ ፊቨር የሚባለው በሽታ አምጪ ተዋህሲያን በቀላሉ እንዲራቡ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል።
|
እና በዚያ በተባሉት ቦታዎች ላይም የአየር ንብረቱም ቆላማ ነው።
|
ለወደፊቱ ደግሞ ምንድነው ምክንያቱ የሚለውን ደግሞ ቀጥለን የምናጠናው ይሆናል ይላሉ።
|
በዴንጊ ፊቨር ላይ የሚደረገው ቀጣዩ ጥናት አሁን በመካሄድ ላይ እንደሆነ አቶ ጌታቸው ይናገራሉ።
|
በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ጥናት ከዚህ ቀደም ከተደረገው ዘርዘር እና ሰፋ ያለ እንደሚሆን ይገልጻሉ።
|
ጥናቱ ከአራቱ የበሽታው አይነቶች የትኞቹ በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ለማወቅ እንደሚረዳ እና በሽታውን ለመከላከል ወደፊት ለሚደረገው ጥረት አንድ መነሻ ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ።
|
እስከ ሞት ሊያደርስ ለሚችለው ዴንጊ ፊቨር ፍቱን መድኃኒት እስካሁን ባይገኝም ተመራማሪዎች ግን የመከላከያ ክትባት መስራታቸውን አስታውቀዋል።
|
ክትባቱን ያመረተው ዓለም አቀፍ ኩባንያ መድኃኒቱ ተጠቃሚዎች ዘንድ እንዲደርስ ለገበያ ያወጣው የዛሬ ሁለት ዓመት ግድም ነው።
|
የዓለም ጤና ድርጅትም በሽታው አዘውትሮ በሚከስትባቸው ሀገራት መድኃኒቱ ጥቅም ላይ መዋል እንደሚችል አዎንታዊ አስተያየቱን ሰጥቷል።
|
በ ሀገራት እውቅና እና ፍቃድ የተሰጠው ይህ ክትባት ከዘጠኝ እስከ ዓመት ላሉ ሰዎች የሚሰጥ እንደሆነ ተገልጿል።
|
ለመሆኑ ዴንጊ ፊቨር እስከ ሞት ሊያደርስ የሚችለው ምን ሲፈጠር ነው
|
የተቃጠሉ መስጊዶች መልሶ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ግዛሉ ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ራድዮ የሮሒንግያዎች ሥቃይ ዓለም አቀፉ ድርጅት ያነጋገራቸዉ ስደተኞች እንደሚሉት የምያንማር ወታደሮች የሮሒንግያ ሙስሊሞችን በጥይት ይገድላሉ ይደበድባሉ መኖሪያ ቤታቸዉን ያቃጥላሉም።
|
እንደሚለዉ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ሌሎች ስደተኞች የምያንማርን ድንበር አልፈዉ ባንግላዴሽ ለመግባት እየሞከሩ ነዉ።
|
ዓለም አቀፉ ድርጅት ያነጋገራቸዉ ስደተኞች እንደሚሉት የምያንማር ወታደሮች የሮሒንግያ ሙስሊሞችን በጥይት እየመቱ ይገድላሉ ሌሎቹን ይደበድባሉ መኖሪያ ቤታቸዉን ያቃጥላሉም።
|
ሊሸከሙት የማይችሉትን ግፍ ሥቃይ እና መከራን የሸሹ ሺሕ ሰዎች እስካሁን ባንግላዴሽ ዉስጥ ከለላ አግኝተዋል።
|
የምያንማር መንግሥት አማፂያንን እዋጋለሁ በሚል ሽፋን በሮሒንግያ ሙስሊሞች ላይ የሚፈፅመዉን ግፍ እንዲያቆም የተለያዩ መንግሥታት ቢጠይቁም እስካሁን ድረስ ተቀባይነት አላገኙም።
|
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሌሎች ማሕበራትም ሆኑ መንግሥታትም በምያንማር መንግስት ላይ እርምጃ ለመዉሰድ አልቃጡም።
|
ተቃውሞ በባሕርዳር ዛሬ በባህር ዳር የክልሉን ገዥ ፓር የሚነቅፍ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በባህር ዳር ተካሂዷል፡፡
|
የአማራዴሞክራሲዊ ፓርተ ስለጉዳዩ አስተያየት እንዲሰጥ ሙከራ ቢደረግም ስብሰባ ላይ ናቸው ስለተባለ አልተሳካም።
|
ባሕር ዳር በአንድ ሳምንት ውስጥ የተለያዩ ዓላማዎችን ያነገቡ ሶስት ሰላማዊ ሰልፎችን አስተናግዳለች፡፡
|
ተመሳሳይ ይዘት ላቸው ሰልፎች በደብረታቦር በጎንደርና በምስራቅ ጎጃም የተለያዩ የወረዳ ከተሞች መካሄዳቸውን የየዞን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች አረጋግጠውልናል።
|
በጉዳዩ ዙሪያ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን አመራሮች የመስተዳድሩን ኃላፊዎች ሀሳብ ለማካትት ያደረግሁት ጥረት ጎንደር ላይ ስብሰባ ናቸው በሚል አልተሳካልኝም።
|
ይህ መጥፎ ውጤት የ ን የበላይ መራኂተ መንግሥት አንጌላ መርክልንም አላስደነገጠም አይባልም።
|
የ ምርጫ ውጤት ለፌደራሉ መንግሥት ምን ዓይነት መልእክት ይሆን የሚያስተላልፈው
|
አፍሪቃ ናሚቢያዊው ሽምቅ ተዋጊ ሔንድሪክ ዊትቦይ አብዛናዎቹ የናሚቢያ ገንዘቦች የተዘረጋ ባርኔጣ ራሳቸው ላይ የደፉ የሔንድሪክ ዊትቦይ ፎቶግራፎች አሏቸው።
|
ሔንድሪክ ዊትቦይ የጀርመን ቅኝ ገዢዎችን ተፋልመዋል ናሚቢያ በአፍሪቃ ከቅኝ አገዛዝ ነጻ በመውጣት የመጨረሻዋ ሃገር ናት።
|
ውይይት የኢትዮጵያ መንግሥት ዉሳኔውን የተቀበለው ከ ዓመት በፊት ነዉ።
|
የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ባለፈዉ ረቡዕ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ መንግሥት የሁለቱን አገሮች ውዝግብ ለማስወገድ ያሳለፈዉን ዉሳኔ እንደሚደግፍ ፍንጭ ሰጥተዋል።
|
ጉዳዩን የሚያጠና የልዑካን ቡድንም ወደ አዲስ አበባ ለመላክ አቅደዋል።
|
የሁለቱ ሃገራት መንግሥታት ሰሞኑን ያሳዩት መቀራረብ ዓመታት ያስቆጠረዉን ጦርነትና ውዝግብ ለማስወገድ ይጠቅማል የሚል ተስፋን አሳድሮአል።
|
ሌሎች ደግሞ የኢህአዴግ መሪዎች የጋራ አቋም መያዝ እንደተሳናቸው ያመላክታል ይላሉ።
|
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ የአልጀርስን ስምምነት በተመለከተ ስለተነሳዉ ተቃዉሞ በያዝነዉ ነው ሳምንት ለም ቤቱ ሰፊ ማብራርያ ሰጥተዋል።
|
በማብራርያቸውም የኢትዮጵያ መንግሥት ስምምነቱንና የድንበር ኮሚሽኑን ዉሳኔ የተቀበለው ከ ዓመት በፊት መሆኑን አመልክተዋል።
|
ስለዚህ የተቃውሞው ምንጭ የአልጀርሱ ስምምነት ሳይሆን ሌሎች ፖለቲካዊና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳዮች ሊሆኑ ይችላሉ የሚለዉን ግምት ይበልጥ እያጎላዉ መጥቶአል።
|
የኢትዮ ኤርትራ አዲስ ግንኙነት የኢህአዴግ ዉሳኔና የህወሓት ተቃዉሞ መወያያ ርዕሳችን ነዉ።
|
የሐረር ገበያ ዳግም እሳት ሐረር ከተማ ዉስጥ በሳምንት ልዩነት ባለፈዉ ቅዳሜ ማታም የእሳት አደጋ መድረሱን ኗሪዎቿ ይናገራሉ።
|
ኢትዮጵያ ድርቅና የእርዳታ ጥሪ በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች ዉስጥ የተከሰተዉን ድርቅ በሚመለከት ተደጋጋሚ ዓለም አቀፍ የርዳታ ጥሪዎች ተደርገዋል።
|
እስካሁን ለችግር የተጋለጠዉ ሕዝብ ከ ሚሊየን በላይ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የእርዳታ ድርጅቶች ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችልም ያሳስባሉ።
|
ኢትዮጵያ ዉስጥ ከ ዓመታት ወዲህ ታይቶ የማይታወቅ በተባለዉ ድርቅ የተጎዱትን ወገኖች ለመርዳት ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
|
የዓለም አቀፍ ለጋሾች እርዳ መዘግየቱን ያመለከተዉ የኢትዮጵያ መንግሥትም ለጋሾች አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጡ አሳስቧል።
|
በርከት ያለ የእህል ምርት ለማፈስ ከጥንት ጀምሮ አርሶ አደሮች የዘር እኽል እየመረጡ በመዝራት አያሌ ዘመናት ጠብቀው ለማቆየት መቻላቸው የሚታበል አይደለም።
|
አንድ ርምጃ ሲወሰድ የሚያስከትለው ጉዳት ምን ሊሆን እንደሚችል ታሳቢ አድርጎ መንቀሳቀስ እንደሚገባ ራሳቸው ከታዘቡት አንድ ታሪክ በመነሣት እንዲህ ይላሉ።
|
ለዚህ ዝግጅት መነሻ የሆነን ባለፈው ሳምንት እንደጠቀስነው በሜክሲኮ ያህል ከአነዚህም ገሚሱ አነስተኛ የመሬት ይዞታ ያላቸው ባቄላ አምራቾች ያነሱት ጥያቄ ነው።
|
በፖላንድ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ብቻ በመጠቀም የሚያመርቱ አርሶ አደሮች ቁጥር ባፋጣኝ በመጨመር ላይ መሆኑ ይነገራል።
|
አዉሮጳና ሕገ ወጥ የሰዉ አሻጋሪዎች ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ጀርመን ስደተኞች እና የመራሒተ መንግሥቷ አቋም ቢያንስ የሰው አመለካከት ለሁለት ተከፍሎአል፡፡
|
አሁንም ቢሆን አንዳዶቹ ከፊታችን የተደቀነውን ችግር እንፈታዋለን እንወጠዋለን ብለው የሚያምኑ ናቸው፡፡
|
ከዚያም አልፈው እንዲያውም እነሱ መራሂተ መንግሥትዋን ይህን እሳቸው ያለፈው ዓመት እንወጣዋልን ያሉትን ቃል ፊት ለፊት አሁን ይቃወማሉ ይተቻሉም፡፡
|
በጀርመን አገር ውስጥ ነገሮች እየተቀያየሩን እየተለዋወጡ እንደመጡ እዚያ እና እዚህ የሚታዩ ፍንጮች በቂ ምስክሮች ናቸው፡፡
|
ጊዜው ተቀይሮ ግን አሁን ለድርጅቱ አመቺ የሆነ ሰዓት የመጣ ይመስላል፡፡
|
እንዲያውም አንዳንዶቹ እዚህ እንደሚሉት የመጠጥና የራት ግብዣ አርዕስትም ሁኖ ብዙ ሰው ሳይፈራ ፊት ለፊት የሚነጋገርበት ጉዳይ ሁኖአል፡፡
|
በሌላ አካባቢ በታላቁዋ ብርታኒያ ለየት ያለ ሥዕል እዚያ እናያለን፡፡
|
እርግጥ ኑዋሪው ሕዝብ በመራሂተ መንግስትዋ ላይ ያለው አመለካከት እንደ አለፉት ጊዜያት ሳይሆን አሁን ተቀይሮአል፡፡
|
እንደ አለፉት አመታት ዘነድሮ መራሂተ መንግሥትዋ ወይዘሮ አንጌላ ሜርክል በሕዝቡ ዘንድ ተወዳጅ አይደሉም፡፡
|
አብዛኛው የጀርመን ሕዝብ ስደተኞቹን አስታኮ የመጣውን ችግር እንፈተዋለን የሚለውን ነገር ሙሉ በሙሉ አምኖ በልቡ አልተቀበለውም፡፡
|
በውጭ ጉዳይ ፖለቲካ ፖሊሲአቸውም ሆነ በሚያቀርቡት አመለካከታቸው መራሂተ መንግስትዋ እንደ አለፉት ዘመናት ዘንድሮም በአዉሮጳ መሪዎች ዘንድ ትልቅ ድምጽና ተቀባይነት አላቸው፡፡
|
ግን ያም ሁኖ ጀርመኖችም በስደተኞች ላይ ያላቸውና የነበራቸው አመለካከት ደግሞ እንዳለ ተቀይሮአል፡፡
|
በመጀመሪያ ቀናት ይታይ የነበረው የእንግዳ ተቀባይነትና የማስተናገድ መንፈስ ቀስ እያለ እየቀዘቀዘና እየበረደ አሁን ሌላ መልክ ይዞአል፡፡
|
ድንበሩ ቢዘጋ ደግሞ በሺህና በአሥር ሺህ በመቶና በሁለት መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ነፍሳቸውን ለማዳን የሚሸሹትን ስደተኞች መርዳት በአልተቻለ ነበር፡፡
|
ትናንሽ ልጆችን የጀርመንኛ ቋንቋ በማስተማር አንዴ የጀመሩትን ሥራ አሁንም ቀጥለውበት ያስተምሩአቸዋል፡፡
|
ብቻቸውን እዚህ የደረሱትን ገና ለአቅመ አዳም ያልደረሱትን ወጣት ልጆች ወስደው እየተንከባከቡአቸው አሁንም ያሳድጉአቸዋል፡፡
|
መሥራት ለሚፈልጉት ሥራ የሙያ ትምህርት ቤት ገብተው ለመማር ለሚፈልጉት ለእነሱም ትምህርት ቤት አብረው ፈልገው እዚያ ይልኩአቸዋል፡፡
|
በሚሊዮን ከሚቆጠሩት አንዱም ስድተኛ መንገድ ላይ ሳያድር ሁሉንም ማስተናገድ በቀላሉ ታይቶ የሚታለፍ ሥራም አይደለም፡፡
|
የሆነው ሆኖ አሁንም ቢሆን ትልቁ ገና ያልተፈታው ችግርም ከፊታችን ተደቅኖ እንደ ቆመም መረሣት የለብንም፡፡
|
እሱም ሕብረተሰቡ የተገን ጠያቂን ስደተኛ ልጆችን ትምህርት ቤት አስገብቶ እነሱን ማስተማር አለበት፡፡
|
ነፍስ ያወቁትን ጎልማሦዎችን እንደዚሁ እነሱን አስተምሮና አሠልጥኖ የሥራ ዓለም ውስጥ ማሰማራትም ይኖርበታል፡፡
|
ይህ ሁሉ ደግሞ ሲሆን ጊዜና ጉልበት ከዚያም በላይ ብዙ ወጪ ገንዘብም የሚጠይቅ ሥራና ኃላፊነት ነው፡፡
|
እዚህ ቀርተው ለመኖር ለሚፈልጉ ስደተኞች የጀርመንን ቋንቋ መማር አላባቸው፡፡
|
ይህ አዲስ ሁኔታ ደግሞ አዲስ ነገር ይዞልን ሊመጣም ይችላል፡፡
|
ቁም ነገሩ ያለው ስደተኞቹን አቅፎና ተቀብሎ እነሱን ከሕብረተሰቡ ጋር በቀላሉ እንዲዋሃዱ መርዳቱ ላይ ነው፡፡
|
ያኔ ነው አብረው እነሱም ጀርመንን በአላቸው ችሎታ ለመገንባት አስተዋጽኦቸውን የሚያበረክቱት፡፡
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.