input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
የሴት ልጅ ግርዛት አዉሮጳን ማስጋቱ የሴት ልጅ ግርዛት በተለያዩ ሃገራት ተግባራዊ እንደሚሆን ሲነገር የቆየ ጉዳይ ነዉ።
|
አሁን አሁን ግን በሰዎች ከሀገር ወደሀገር መዟዟር ምክንያት ቀድሞ በማይታወቅበት አካባቢ ሁሉ እየተዳረሰ መሆኑ እየተነገረ ነዉ።
|
አዉሮጳ ዉስጥ በልማድም ሆነ በባህል ያልነበረዉ ይህ ድርጊት ዛሬ የበርካቶች ስጋት ከሆነ ሰነባበተ።
|
መረጃዎች እንደሚያመለክቱ አዉሮጳ ዉስጥ በየዓመቱ ታዳጊ ሴቶች ለግርዛት ይጋለጣሉ።
|
ይህን ጎጂ ልማድ ለመግታት የሚንቀሳቀሱ ተቋማትም የአዉሮጳ ኅብረት የተጠናከረ ርምጃ እንዲወስድ ግፊት እያደረጉ ነዉ።
|
አዉሮጳ ዉስጥ ስዊድን ናት በመጀመሪያ ሴት ልጆች ግርዛት እንዳይፈጸምባቸዉ በህግ የደነገገች አገር።
|
በጎርጎሪዮሳዊዉ ዓ ም በመሠረቱት ጎበዝ በተሰኘዉ ተቋም አማካኝነትም የባህል ልዉዉጥና ማኅበራዊ እንዲሁም ጤና ነክ ጉዳዮችን የሚመለከቱ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋሉ።
|
ጎበዝ የተሰኘዉ ተቋም በተለይ የሴቶችን ጤንነት በሚመለከት የሴት ልጅ ግርዛት እንዲቆም የበኩሉን ጥረት እንደሚያደርግ ነዉ የተረዳነዉ።
|
የኔዘርላንድ መንግስት ግን መረጃ ማዳረሱንና ለቤተሰቦችም ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ገፍቶበታል በነገራችን ላይ በዚህ አገልግሎት ከሚሳተፉ ሶስቱ የኔዘርላንድ ዜጎች ናቸዉ።
|
የሚያስከትለዉ ስቃይም በወቅቱ ሲፈጸም ብቻ ሳይሆን ለአንዳንዶች የእድሜ ልክ መሆኑንም የደረሰባቸዉን በእማኝነት የሚጠቅሱ መረጃዎች ሞልተዋል።
|
ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ በተለያዩ እርከኖች በሚገኙ የመንግሥት መዋቅሮች ስቅየት ይፈጸም እንደነበር ተናግረዋል።
|
ምንም ይሁን ማን ሕገ መንግሥትን ማክበር አለበት የሚል እሳቤ መያዝ ያስፈልጋል።
|
ኃላፊነትን የሚሰማን መንግሥት ስንሆን ደግሞ የዚህ ጉዳይ መዛነፍ ኃላፊነት መውሰድ ያለብን እኛ ነን ብለዋል።
|
ሕገ መንግሥቱ የደኅንነት ተቋማት መከላከያውን ጨምሮ ከፓርቲ ገለልተኛ ሆነው ሕግ እና አገር የሚጠብቁ መሆን አለባቸው ብሎ ያስገድዳል።
|
ሲሉ የጠየቁት ጠቅላይ ምኒስትሩ እንደዛ ካላደራጀንው ኢ ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ተቋም ፈጥረናል ማለት ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
|
ሕገ መንግሥቱ በፍርድ ቤት የታሰረ ሰው ግረፉ ጭለማ ቤት አስቀምጡ ይላል እንዴ
|
ይኼን ሕገመንግሥታዊ ያልሆነ ድርጊት በእያንዳንዱ ቀበሌ በእያንዳንዱ ወረዳ በእያንዳንዱ ዞን ሲፈጸም ቆይቷል።
|
ጠቅላይ ምኒስትሩ ነፍጥ አንግበው መንግሥታቸውን ለመጣል ኤርትራ የገቡ ተቃዋሚዎች እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል።
|
ጠቅላይ ምኒስትሩ በንግግራቸውም ሆነ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቀረቡላቸው ጥያቄዎች ኢትዮጵያ የገጠሟትን አንገብጋቢ ጉዳዮች አንስተዋል።
|
የአገራቸው ኤኮኖሚ የገጠመውን ፈተና የፖለቲካውን ውጥንቅጥ የፍትኅ ሥርዓቱን ችግሮች ስለ ሙስናና በተለያዩ አካባቢዎች ስለሚታዩ ግጭቶች ማብራሪያ አቅርበዋል።
|
ጠቅላይ ምኒስትሩ እንዳሉት በ ዓ ም የመጀመሪያ ስድስት ወራት ብቻ ኢትዮጵያ ሚሊዮን ዶላር ለዕዳ ስትከፍል ቢሊዮን ዶላር ተበድራለች።
|
አጠቃላይ የአገሪቱ የብድር መጠን ደግሞ ወደ ቢሊዮን ዶላር አሻቅቧል።
|
የሁለቱ ሐገራት ባለሥልጣናት ግን የሥምምነቱ ይዘት በተደጋጋሚ ጋዜጣዊ መግለጫ መብራራቱ እና በዓምደ መረብ መሰራጨቱን ይናገራሉ።
|
አፍሪቃ የአንጎላ ምርጫ ዘመቻ አንጎላ ከ ቀናት በኋላ አዲስ ምክር ቤት እና አዲስ ፕሬዚደንት ትመርጣለች።
|
በጎርጎሮሳዊው ዓ ም ስልጣን ላይ ሲመጡ አንጎላ ከፖርቱጋል ቅኝ አገዛዝ ተላቃ ነፃነቷን ካገኘች ገና አራት ዓመቷ ነበር።
|
በአንጎላ የርስበርሱ ጦርነት ከ ዓመታት በኋላ ምርጫው በ ዓም ተካሂዷል።
|
የያኔው ምርጫ በሀገሪቱ ከዚያን ጊዜ በኋላ እንደተካሄዱት ምርጫዎች ሁሉ ፕሬዚደንት ዶሽ ሳንቶሽን እና ፓርቲያቸው አሸናፊዎች ሆነዋል።
|
የተቃዋሚ ወገኖች ምርጫቹን እኩል እድል ያላገኙባቸው እና የመንግሥት የማጭበርበር ተግባር የታየባቸው ነው በሚል በጥብቅ ይነቅፋሉ።
|
ይሁንና ምርጫውን የታዘቡ ዓለም አቀፍ ቡድኖች የምርጫውን ውጤት ሲቀበሉ ነው የታዩት።
|
በዘንድሮው የአንጎላ ምርጫ በመዲናይቱ ሉዋንዳ ለሚገኙት የምክር ቤት መንበሮች ስድስት ፓርቲዎች በተፎካካሪነት ቀርበዋል።
|
በምርጫው ውጤት የአብላጫውን ድምፅ በሚያገኘው ፓርቲ የእጩዎች ስም ዝርዝር ላይ ስሙ በአንደኛነት የሚቀርበው እጩ የሀገሪቱ ርዕሰ ብሔር ይሆናል።
|
በዘንድሮው ምርጫ አንድ በግልጽ የሚታወቅ ጉዳይ ቢኖር ፕሬዚደንት ኤድዋርዶ ዶሽ ሳንቶሽ የሀገሪቱ መሪ እንደማይሆኑ ነው።
|
በምርጫው እንደማይወዳደሩ ቀደም ሲል ካስታወቁ በኋላ ፓርቲው በመጨረሻ ባካሄደው ጉባዔው ዦዋዎ ሉሬንቾን ቀዳሚው እጩ አድርጎ ሰይሟል።
|
ከምርጫው በኋላ ሉሬንቾ ቀጣዩ የአንጎላ ፕሬዚደንት መሆናቸው እንደማይቀር ማንም አልተጠራጠረም።
|
የተቃዋሚ ወገን በአሁኑ ጊዜም ቢሆን በቂ የማሸነፍ እድል የለውም።
|
እርግጥ በወቅቱ በሚታየው ከፍተኛ የህዝብ ብሶት የተነሳ የተቃዋሚ ወገን ከገዢው ፓርቲ የተወሰነ ድምፅ መንጠቁ አይቀርም።
|
ይሁን እንጂ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የተከፋፈሉ እና ጠንካራ መሪም የሌላቸው ናቸው።
|
ምን ለመስራት እንደሚፈልጉም መልዕክታቸውን ለህዝብ በሚገባ መልኩ ማስተላለፍ አልቻሉም።
|
እስካሁን እንደሚታየው በሀገሪቱ ያሉት ፓርቲዎች እኩል የመፎካከር እድል አላቸው ሊባል አይችልም።
|
እርግጥ ሁሉም ፓርቲዎች በመንግሥት ራድዮ እና ቴሌቪዥን ማስታወቂያዎቻቸውን ማስተላለፍ ይችላሉ።
|
ይህ ግን ብቸኛው ምሳሌ ነው ከዚህ በተረፈ ግን ፓርቲዎች በጠቅላላ በአንድ ዓይን ታይተው እኩል እድል ይሰጣቸዋል ብሎ ማሰቡ ስህተት ነው።
|
ምክንያቱም ይላሉ የፓርቲው የውጭ ጉዳይ ተጠሪ ንቱ ሁሌም ሲደረግ እንደቆየው ገዢው ፓርቲ ከሌሎቹ በተለየ ለራሱ ሰፊ እድል ሰጥቶዋል።
|
ቴካ ንቱ ካለፉት ዓመታት ወዲህ በጀርመን የኤሰን ከተማ ሲሆን የሚኖሩት ለምርጫው ዘመቻ እረፍት ወስደው ወደ አንጎላ ሄደዋል።
|
ባለፉት ምርጫዎች የተቃዋሚው ወገን በጠቅላላ ከ የምክር ቤት መንበሮች መካከል ዎቹን እንኳን አለማግኘቱ በጣም የሚያሳዝን ነው።
|
ብዙ የፖለቲካ ታዛቢዎች እንደሚገምቱት በምርጫ ዘመቻ ወቅት ብዙም የማይታዩት የአንጎላ ፕሬዚደንት ዶሽ ሳንቶሽ በጠና ሳይታመሙ አልቀሩም።
|
የፖርቱጋል ሳምንታዊ መጽሄት ኤስፕሬሶ ታማኝ ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው እየተበላሸ የሄደው የፕሬዚደንቱ ጤንነት የአንጎላ አመራር አባላትን እጅግ አሳስቧል።
|
ርዕሰ ብሔሩ ፕሬዚደንቱ አንድ ነገር ቢሆኑ ይህ ለ ኤምፒኤልኤ ድንገተኛ አይሆንበትም የዶሽ ሳንቶሽን ተተኪ በማዘጋጀት ዦአዎ ሉሬንሶን መርጧል።
|
በመሆኑም ፕሬዚደንቱ ድንገት በምርጫ ዘመቻ ወቅት እንኳን ቢሞቱ ፓርቲው ችግር አያጋጥመውም።
|
ከፍተኛ የመንግሥት ቦታዎችን ለመያዝ የስልጣን ሽኩቻ ሊነሳ ይችላል ባይ ናቸው።
|
ምክንያቱም ኾዜ ኤድዋርዶ ዶሽ ሳንቶሽ ዋና ዋና የሚባሉትን የመንግሥት ስልጣን ቦታዎችን ለርሳቸው ታማኝ ለሆኑ ሰዎች ሰጥተዋል።
|
ለምሳሌ ልጃቸው ኢዛቤል ዶሽ ሳንቶሽ የሀገሪቱን የነዳጅ ዘይት ተቋም ሶናንጎልን ወንድ ልጃቸው የመንግሥቱን የነዳጅ ዘይት መስሪያ ቤትን በኃላፊነት ይመራሉ።
|
የፖሊስ የጦር ኃይሉ እና የስለላ ድርጅቱም በዶሽ ሳንቶሽ ታማኞች ነው የተያዘው።
|
እነዚህ ባለስልጣናት ዶሽ ሳንቶሽ ስልጣናቸውን በሚለቁበትም ጊዜ ይህንኑ ስልጣናቸውን እንደያዙ መቆየት ይችላሉ።
|
የአንጎላ ምክር ቤት በመጨረሻው ጉባዔው ወቅት ተሰናባቹ ፕሬዚደንት የሾሟቸው ባለስልጣናት እንዳይነኩ የሚያዝ አንድ ህግ በከፍተኛ ድምፅ አፅድቋል።
|
ህጉን በምክር ቤት የሚወከሉት ሁለቱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ዩኒታ እና ካዛ ሲኤ ቢቃወሙትም ከ የምክር ቤት መንበሮች ብቻ በመያዛቸው ሕጉ አልፏል።
|
የሕጉ ማለፍ በጣም አነጋጋሪ እንደነበር ዜጠኛ ኾዜ አዳልቤርቶ አስታውሷል።
|
ኤድዋርዶ ዶሽ ሳንቶሽ ፕሬዚደንቱ ትተውልን የሚሄዱት ሕግ ብዙ ክርክር አስነስቶ ነበር።
|
እና ለጦር ኃይሉ ለፖሊሱ እና ለስለላው ተቋም የሚፈልጓቸውን ሰዎች መሾም ይፈልጋሉ ብዬ ነው የማስበው።
|
የአፍሪቃ ዋንጫ አስተናጋጅ ለሳምንታት የዘለቀ ደም አፋሳሽ አመፅ መካከለኛው አፍሪቃ የምትገኘው ሀገር ብሩንዲን አጨናንቋል።
|
የሀገሪቱ ጦር ከአማፂያን ጋር እየተታኮሰ በርካታ ሰዎች መሞታቸውም ተረጋግጧል።
|
ከዚህም በተጨማሪ ማንነታቸው ያልታወቁ እና የወታደር የደንብ ልብስ የለበሱ ሰዎች በርካታ የመንግሥት ፓርቲ አባሎችን መግደላቸው ተሰምቷል።
|
በሚመጣው ግንቦት እና ሰኔ ወር ብሩንዲ ውስጥ ምክር ቤታዊ እና ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይካሄዳል።
|
የገዢው ፓርቲ መሪ ፒር ንኩሩንዚዛ ለሶስተኛ ዙር በፕሬዘደንትነት እቀርባለው ማለት ግጭቱን ይበልጥ አፋፍሞታል።
|
የብሩንዲ ህገ መንግሥት ለአንድ መሪ የስልጣን ዘመን ቢበዛ የምርጫ ዙር ነው ያስቀመጠው።
|
ጥቃቶች ሲፈፀሙ የሚታየው ልክ በገዢው ፓርቲ እና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ግጭት ሲነሳ ነው።
|
እንደ ቦኒምፓ ተቃዋሚዎች ገዢው መንግሥት የምርጫ ምዝገባውን እያጭበረበረ ነው ብለው ያምናሉ ይላሉ።
|
የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቦኒምፓ ሲቪል ማሕበረሰቡም ቢሆን በምርጫው የምዝገባ አሠራር ደስተኛ እንዳልሆነ ነው የሚናገሩት።
|
ሆን ተብሎ ተቃዋሚዎችን ለማስፈራራት እና ለማሸማቀቅ ሲባል ፍተሻ ይካሄድ ነበር።
|
የመብት ተሟጋቹ ቦኒምፓ መንግሥትን የሚቃወም አስተያየት በመስጠታቸው ታስረው እንደነበር ይናገራሉ።
|
ጋዜጠኞችም ቢሆኑ ነፃነት እንደሌላቸው እና ለህይወታቸው እንደሚሰጉ ነው የሚናገሩት።
|
የተባለው የተቃዋሚዎች የሬዲዮ ጣቢያ ባልደረባ የሆነ አንድ ጋዜጠኛ ለዶይቸ ቬለ እንደተናገረው በቅርቡ ከተጣለበት ጥቃት ለጥቂት ነው የተረፈው።
|
የመካከለኛው አፍሪቃ የግንኙነት መረብ ባልደረባ ጌዚነ አሜስ ለተቃዋሚዎች እና የመብት ተሟጋቾች የመፈናፈኛው እድል እጅግ ውስን ነው።
|
ይህም ማለት ሀሳብ የመስጠት እና የመሰብሰብ መብታቸው የቀነሰ ነው።
|
መንግሥት ደግሞ በሲቪል ማህበረሰብ እና የመብት ተሟጋቾች ላይ ጭቆናውን ቀጥሏል።
|
በዛ ላይ መንግሥት እና ተቃዋሚዎች አንድ ዓይነት ህግ የላቸውም ይላሉ።
|
ይህም ግልፅ የሚሆነው ለምሳሌ ተቃዋሚዎች ልክ ከምርጫዎቹ ሁለት ሳምንታት አስቀድመው ብቻ ነው የመሰብሰብ እና የምርጫ ዘመቻ የማካሄድ መብት ያላቸው።
|
ይልቁንስ ተቃዋሚዎች የምርጫ ሂደቱን ሊያበላሹ ብሎም መንግሥትን ሊገለብጡ ነው የተነሳሱት።
|
ይህም በዚህ ላይ የሚደረገው አፀፋ አመፅ ማስነሳቱን ለማየት ነው።
|
እንደ ጌዚነ አሜስ ብሩንዳዊያኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ መንግሥት ቃል የሚገባውን እንደማይወጣው ተገንዝበዋል።
|
አሜስ ህዝቡ ምርጫ አድክሞታል ይህ ግን የግድ በመንግሥት ምክንያት ብቻ አይደለም ይላሉ።
|
እና የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የሀገሪቱን ከመቶ ማስተዳደሪያ እንደሚሸፍን ለማስታወስ እወዳለሁ።
|
ጌዚነ አሜስ ደግሞ የአውሮፓ ሕብረት አንድ አይነት ርምጃ ያስፈልገዋል ባይ ናቸው።
|
የብሩንዲን ወቅታዊ ልማት ወጥ ለማድረግ የአውሮፓ ህብረት አንድ አይነት ውሳኔ ያስፈልጋል በግልፅ የፕረስ ሀሳብን በነፃ የመግለፅ እና የመሰብሰብን ነፃነት የሚጠይቅ።
|
በተለይ የሀገሪቱ መንግሥት ዝግጅቱን ከጥሩ ገፅታው ብቻ ለማሳያ እየተጠቀመበት እንደሆነ የመብት ተሟጋቾች ይናገራሉ።
|
ተረኛ የነበረችው ሞሮኮ ባለፈው ህዳር ወር ነበር በምዕራብ አፍሪቃ የተዛመተውን ገዳዩን የኤቦላ ቫይረስ ፍራቻ ውድድርን እንደማታዘጋጅ ያስታወቀችው።
|
በአለም አቀፍ ዘንድ ገፅታውን ለመቀየር ሲሞክር ይህ የመጀመሪያው ጊዜ አይደለም ይላሉ ከሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምንስቲ ኢንተርናሽናል ቪክቶር ኖጉሪያ ።
|
እንደ አምንስቲ ኢንተርናሽናል ያሉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለዓመታት የኤኳቶሪያል ጊኒን መንግሥት የሰብአዊ መብትን አያከብርም ሲሉ ተችተዋል።
|
ልዩ ለግድያ የተዘጋጀ ቦታ አለ ከዚህም በተጨማሪ የፕረስም ሆነ ሀሳብን በነፃ የመግለፅ መብት የተጨቆነ ነው።
|
አምንስቲ ኢንተርናሽናል ባለፉት አመታት የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ክስ ሳይመሰረትባቸው በዘፍቃድ እየታሰሩ እና እየተገረፉ ነው ሲል ዘግቧል።
|
እንደዚሁ ድርጅት ዘገባ ባለፈው ዓመት መጋቢት ወር ቢያንስ አራት እስረኞች ተገድለዋል።
|
ኤኳቶሪያል ጊኒ ለሁለት ሳምንታት ያክል ብቻ ነው የሞት ብይኗን ያቋረጠችው።
|
ይህም የፖርቹጋል ቋንቋ ተናጋሪ ሀገራት ማህበረሰን ለመቀላቀል መስፈርቶችን ማሟላት ስለነበረባት እንደሆነ ይነገራል።
|
የተፈጥሮ ሀብትን በተመለከተ ኤኳቶሪያል ጊኒ በዘይት እና በጋዝ ከአፍሪቃ ሀብታም ከሆኑት ሀገራት ተርታ ትመደባለች።
|
የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከጥሬ ሀብት የውጭ ገበያ የሚገኘውን ገንዘብ ለራሳቸው በግል ባንካቸው እንደሚያስገቡ ይተቻሉ።
|
ሀገሪቱ የዘይት ሀብት ስላላት የህዝቡ የነፍስ ወከፍ ገቢ ከሌሎች የአፍሪቃ ሀገራት ጋር ሲነፃጸር በአማከይ ከፍተኛ ነው።
|
ይላሉ ከሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ኖጉሪያ እኢአ ከ ዓም ጀምሮ ፕሬዚዳንት ቴውድሮ ኦቢያንግ ንጉማ ሀገሪቱን ይመራሉ።
|
የመብት ተሟጋቹ እንደሚሉት ፕሬዚዳንቱ ይህንን አጋጣሚ ለጥሩ ስም እየተጠቀሙበት ነው።
|
ነገር ግን በሌላ በኩል ስላለው የሀገሪቱም ገፅታ ትኩረት እንዲሰጥ ይጠቅማል።
|
ነገር ግን ጋዜጠኞች በዚህ ጉዳይ ላይ ፍላጎቱ ካላቸው በሀገሪቱ ትኩረት ስላላገኘው ነገር ሊዘግቡ ይችላሉ።
|
በርግጥ የዘንድሮው የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር አዘጋጅ ሀገር ኤኳቶሪያል ጊኒ ከዚሁ ዝግጅት በምን እንደምትጠቀም በቀጣዩ ሳምንታት የሚታይ ይሆናል።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.