input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ድዋሌ ያሉትን ከማለታቸዉ ከብዙ ዓመታት በፊት የሶማሌዎችን መገዳዳያ ትልቅ እስር ቤት ጥሩ ሐገር ለማድረግ ብዙ ተሞክሮ ነበር።
|
የጨረሻዉ ጉባኤ ቃል ዛቻ ከቀድሞዋ የሶማሊያ ቅኝ ገዢና የበላይ ጠባቂ ርዕሠ ከተማ ተሰማ።
|
እንደ ወታደር ሱዳን ዘመተዉ ለሱዳን ነፃነት የሚፋለሙ አማፂያንን ወግተዋል።
|
እንደ ሚንስትር ሶማሊያ ሲገቡም ፓኪስታንም ሱዳኑም የሐገራቸዉን ጦር ሲወጉ ያዩቸዉ ሙስሊሞች ቅኝ ገዢ ጦራቸዉን ሲወጉ አዩ።
|
የብሪታንያ የኋላ ተወዳጅ ጠቅላይ ሚንስትር ለየቅኝ ተገዢዎቹ ሐገራት መዉደም ተጠያቂዎቹ ቅኝ ገዢዎች ሳይሆኑ እስልምና ነዉ ብለዉ አረፉ።
|
ይህንን እምነታቸዉን ዘ ሪቨር ዎር ባሉት መፅሐፋቸዉ በሰፊዉ አተተቱት።
|
ባለፈዉ ሳምንት ሐሙስ ለንደን ላይ የመከረዉን ዓለም አቀፍ ጉባኤ የመሩት ጠቅላይ ሚንስትር ቴሬሳ ሜይ የቸርችል ፓርቲ መሪ ናቸዉ።
|
ምናልባት ፖለቲካዊ ሥብዕናቸዉንም አድናቂ ሊሆኑ ይችላሉም ለጉባኤተኞች የነገሩት ግን የሶማሊያ ቀዉስ በጣም እንዳሳሰባቸዉ ነዉ።
|
ይሕን ያክል የዓለም ማሕበረሰብ ተወካዮች እዚሕ አዳራሽ መገኘታቸዉም ሶማሊያን ማረጋጋት አስፈላጊ እንደሆነ ሥላመኑበት ነዉ።
|
ተገቢዉን እርምጃ እንደምንወስድ ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ የምንገነባዉም የረጅም ጊዜም ትንሳኤ ተስፋ እንደሚሆን ማረጋገጥ አለብን።
|
ሰኔ ጁቡቲ ላይ እንዲሕ እንዳሁኑ በሶማሊያ ጉዳይ ላይ የተነጋገረ ጉባኤ ነበር።
|
ዓላማዉ ለሶማሊያን ማዕከላዊ መንግሥ መመሥረት ሐገሪቱን ማረጋጋት ሕዝቧን መርዳት የሚል ነበር።
|
የፕሬዝደንት ዓሊ መሕዲ መሐመድ የመልዕክተኞች ቡድን ሞቃዲሾ በገባ ማግሥት ጁቡቲ ላይ የተባለ የታቀደ ቃል የተገባዉ ሁሉ በነበር ቀረ።
|
ከጅቡቲዉ እስከ ሐሙሱ ጉባኤ ድረስ ከጅቡቲ ሁለት እስከ ናይሮቢ ከካይሮ እስከ ብራስልስ ከአዲስ አበባ እስከ ለንደን ጉባኤዎች ተደርገዋል።
|
ለንደን ዉስጥ ብቻ በ እና በ ሁለት ጉባኤዎች ተደርገዋል።
|
ዉጤቱ አንዲቷን ሐገር የሶማሊያ ዴሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ የሶማሊ ላንድ የፑንት ላንድ የጋልሙዱግ የአዛኒያ ወደሚባሉ ትናንሽ ሐገር ወይም መንግሥትነት መከፋፈል ነዉ።
|
ከ ጀምሮ የተደረገዉ ጉባኤ ሥብሰባ የጦር ዘመቻ ርዳታ በጥፋት ዉጤት የተጣፋዉም ሶማሌዎች ሠላም ሥለማይፈልጉ አይደለም።
|
ሶማሊ ላንድ ከቀድሞ ቅኝ ገዢዋ ዋና ከተማ ለንደን ዉስጥ ቆስላ ከፍታለች።
|
አንድ ሰሞን የዩናይትድ ስቴትስ ጦር የሶማሊላንድ ወደብን በግልፅ ይጠቀም ነበር።
|
የአረብ ሐገራት ከሶማሊላንድ ጋር ከጦር ሰፈር እስከ ንግድ የሚደርስ ግንኙነት አላቸዉ።
|
ዩናይትድ ስቴትስ አረቦችም ሆኑ ኢትዮጵያ ሶማሊ ላንድን እንደ መንግሥት አያዉቁትም።
|
አብረዋት ለሚሰሯት ሐገር የመንግስትነት እዉቀና ያልሰጡበት ምክንያት በርግጥ ያነጋግራል።
|
ሶማሌን ሠላም ለማድረግ ከሶማሌዎች መሐል የመሐመድ አብዱላሒ መሐመድ መንግሥትን መርጦ ወዳጅን ማስታጠቅ አሸባብን ነጥሎ በሞቃዲሾ መንግሥት ማስመታት ነዉ።
|
ከዚሕ በፊት ከ ጀምሮ ተሞክሮ መክሸፉ እንደገና ተደግሞ እንደገና መጨናገፉ እንጂ ድቀቱ።
|
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተረሽ እንደሚሉት ዘንድሮም ረሐብ እያንዣበበ ነዉ።
|
ከ ሺሕ የሚበልጡ ሕፃናት ደግሞ ለሕይወታቸዉ በሚያሰጋ ረሐብ እየተሰቃዩ ነዉ።
|
የበለፀገዉ ዓለም ዘግይቶም ቢሆን ረሐብተኛዉን ሕዝብ እንደሚረዳ በለንደኑ ጉባኤ ላይ ቃል ገብቷል።
|
ከሶማሌዎች መሐል ታማኝ ሶማሌዎች የተጋበዙበት ጉባኤ ያሳለፈዉ ዉሳኔ የጦርነት ረሐብ ዑደቱን ማስቀረት መቻሉ ግን ሲበዛ አጠራጣሪ ነዉ።
|
የቀድሞዉ የሶማሊላንድ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር አብዱላሂ መሐመድ ዱዋሌ እኛ ጨቅላ ዴሞክራሲን እየተንከባከብን ነበር ይላሉ ዓለም ግን ጀርባችንን ይዠልጠናል።
|
የጀርመን መራሒተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል እና የፈረንሳይ ፕሬዚደንት ኤማኑዌል ማክሮ አዲስ የጀርመን እና ፈረንሳይ ወዳጅነት ውል ተፈራረሙ።
|
ሜርክል እና ማክሮ አገሮቻቸውን በሚያዋስነው ኪሎ ሜትር ርዝመት ባለው ድንበራቸው የሚካሄደውን የጋራ ትብብር ማሳደግ ፍላጎት አላቸው።
|
ይህ በመሆኑም አንደኛ በአውሮጳ ህብረት ውስጥ ጀርመን እና ፈረንሳይ የያዙትን ኃላፊነት እንደአዲስ መመልከት አለብን።
|
ሶስተኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ በጋራ ርምጃ መውሰድ በሚያስችለን የጋራ ሚና ላይ መግባባት ላይ መድረስ ይኖርብናል።
|
የቤልጂየም ፖሊስ በጂሃዲስትነት የጠረጠራቸዉን ሁለት ከሶሪያ የተመለሱ መሆናቸዉ የተገለጸ ጥቃት አድራሾች ሲገድል አንዱን በቁጥጥር ሥር ማዋሉ ተነግሯል።
|
ፖሊስ የሽብር እቅዱን ያከሸፈዉ ከብራስልስ መቶ ኪሎሜትር ርቀት ላይ ከጀርመን ድንበር አቅራቢያ በምትገኘዉ የቨርቬርስ ከተማ ባካሄደዉ አሰሳ ነዉ።
|
የቤልጂየም ጠቅላይ ሚኒስትር ፖሊስ የወሰደዉ ርምጃ መንግሥታቸዉ ሽብርን ማስፋፋት የሚሹትን ለመዋጋት መቁረጧን ያሳያል ብለዋል።
|
ባለፈዉ ሳምንት ፓሪስ ላይ ከደረሰዉ የሽብር ጥቃት በኋላ ጀርመንን ጨምሮ አብዛኞቹ የአዉሮጳ ሃገራት ከፍተኛ ጥንቃቄና ቁጥጥራቸዉን አጠናክረዋል።
|
በኬሚሴ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሒዷል ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
የወታደሮቹ ተልዕኮ በመንግሥቱ ጦር እና በዓማፅያን መካከል የሚካሄደው ውጊያ ዒላማ ያደረገው የአካባቢው ሲቭል ሕዝብ ጉዳት እንዳይደርስበት መከላከል እንደሆነ አንሚስ አመልክቷል።
|
ስለአሳሳቢው ሁኔታም ከተቃዋሚ ቡድኖች መሪዎች እና ከመንግሥት ተወካዮች እንዲሁም በወዝግቡ አብዝተው ከተጎዱት ተፈናቃዮች ጋር ተወያይተዋል።
|
ሎውኮክ በማዕከላይ ኢኳቶርያ ግዛት ያነጋገሯቸው የተቃዋሚው ኤስፒኤልኤ አይ ኦ ተጠባባቂ መሪ ፒተር ሊዦ ጆሴፍ ለሕዝብ መቆሙን አረጋግጠውላቸዋል።
|
ሕዝቡ የድርድሩ ማዕከል በሚሆንበትም ጊዜ በሀገሪቱ ሰላም እንደሚወርድ እርግጠኞች ነን።
|
የነፍስ ግድያ እና ክብረ ንፅህና መድፈርን እንደ ጦር መሳሪያ የጠቀሙባቸዋል።
|
እነዚህ ሁሉ ዓለም አቀፍ ሕጎችን የጣሱ ግዙፍ ወንጀሎች ናቸው።
|
በአሁኑ ጊዜ ሰባት ሚልዮን ሕዝብ የሰብዓዊ ርዳታ ያስፈልገዋል ሁኔታዎችም እየከፉ በመሄድ ላይ ናቸው።
|
በመሆኑም ውዝግቡ የሚመለከታቸው ሁሉ ሰላም ለማውረድ እንዲጥሩ ዓለሙ መንግሥታት ድርጅት ባለስልጣን ማርክ ሎዎኮክ ተማፅነዋል።
|
በሀገሪቱ የሚታየውን ሰብዓዊ ስቃይ ለመቀነስ የኃይሉን ተግባር ማብቃት የመጀመሪያው እና ብቸኛው ዋነኛ ጉዳይ ይሆናል።
|
ስለዚህ የሚያስፈልገን ወደ ርዳታ ፈላጊው ሕዝብ መድረስ የምንችልበት ፈጣን አስተማማኝ እና ገደብ ያላረፈበት መንገድ ነው።
|
የአፍሪቃ ህብረት በየቀኑ ሲብሎችን የሚገድሉትን ወይም ሲብሎች ለሚገደሉበት ድርጊት ድርሻ የሚያበረክቱትን ለመቅጣት በሚወስደውን ርምጃ አንጻር መቆም ለማንም ቢሆን ትክክለኛ አይደለም።
|
የአፍሪቃ ህብረት ከኢጋድእና ከሌሎች አጋሮች ጋር ባንድነት በመሆን ሰላም ለማውረድ የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፉትን ለመቅጣት ሳያመነታ እና ሳያሰልስ መስራቱን ይቀጥላል።
|
ድርድሩን በሸምጋይነት እየመራ ያለው ኢጋድ የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኞች የፈረሟቸውን የሰላም ስምምነቶች እንዲያከብሩ ጥረት ቢያደርግም እስካሁን አልተሳካለትም።
|
እንዲሁም ሌላው ደግሞ የስልጣን ክፍፍሉ ተመጣጣኝነት ብሎም የካቢኔው አደላደል ሶስተኛው በሀገሪቱ የሚኖሩት ግዛቶች ቁጥር ይጠቀሳሉ።
|
ምን ያህል ግዛቶች ሊኖሩ ይገባል የሚለውን ጥያቄ በተመለከተ አንዳንዶች ሲሉ መንግሥት ብሏል ይህ ጉዳይ መፍትሔ ሊገኝለት ይገባል።
|
ሌላው የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኞችን እያወዛገበ የሚገኘው ጉዳይ የፀጥታውን ጥያቄ ይመለከታል።
|
የሀገሪቱ መንግሥት ዓማፅያን ቡድኖች በብሔራዊው ጦር ውስጥ እንዲዋኃዱ ሲጠይቅ ተቃዋሚዎች የመንግሥቱ የኤስፒኤል ጦር ተበትኖ አዲስ ጦር እንዲቋቋም ነው የሚፈልጉት።
|
በድርድሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ሱዳን አንግሊካን ቤተ ክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ጃስቲን ባዲአራማ ተቀናቃኞቹ ወገኖች ልዩነታቸውን በማስወገድ ውዝግቡን ባፋጣን እንዲያበቁ አሳስበዋል።
|
እና ሕዝባቸውን የሚወዱ ከሆነ ሕዝቡ ከመጥፋቱ በፊት የሕዝቡን ፍላጎት በማድመጥ ሰላምን መቀበል አለባቸው።
|
ይዘት ሼክ አንታ ዲዮፕ በርካታ የአፍሪካ ሃገራት ነጻነታቸውን በመቀዳጃቸው ዋዜማ በአህጉሪቱ በሚገኙ አብዛኞቹ ምሁራን ዘንድ አንድ መጽሐፍ ተወዳጅ ነበር።
|
መጽሐፉ የኔግሮ ሃገራት እና ባህል በሚል ርዕስ በሴኔጋሊያዊው ሼክ አንታ ዲዮፕ የተከተበ ነው።
|
በርካታ መጽሐፍትን ላሳተሙት ፕሮፌሰር አንታ ዲዮፕ ይህ የመጀመሪያ መጽሐፋቸው ነው።
|
ፕሮፌሰሩ ከዘረኝነት ጭፍን ጥላቻ የተላቀቀ አጠቃላይ የአፍሪቃ ታሪክን የመጻፍን መንገድ የከፈቱ ናቸው ይባልላቸዋል።
|
አዲስ አበባን ያስጨነቀው እስርና መግለጫ ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
የምርጫ ቅስቀሳ በደቡብ ክልል የምርጫ ምልክቶችን የያዘዉ የናሙና ፖስተር በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች አለመለጠፉንም መድረክ አክሎ ገልጿል።
|
የኤርትራ ኛ ዓመት የነፃነት ዕለት ኤርትራ ተቺዎች እንደሚሉት አሁን የአፍሪቃ ሰሜን ኮሪያ ናት።
|
ድንበር የለሽ ዘጋቢዎች በቅርቡ ባወጣዉ የፕረስ ነፃነት ዝርዝር ከኤርትራ የባሰች ሐገር ብትኖር አንድ ናት።
|
ኤርትራ ከኢትዮጵያ ተገንጥላ የራስዋን መንግሥት በይፋ ከመሠረተች ዛሬ ዓመት ደፈነች።
|
የቀድሞዎቹ አማፂያን የመሠረቱት መንግሥት ትንሺቱን ምሥራቅ አፍሪቃዊት ሐገር የመላዉ አፍሪቃ የልማት ዕድገት አብነት እንደሚያደርጓት ተስፋ ሰጥተዉ ነበር።
|
ተስፋዉ ግን የዶቸ ቬለ ዳንኤል ፔልስ እንደዘገበዉ ብዙ አልቆየም።
|
ኤርትራ ዛሬ ብዙ ተንታኞች እንደሚተቹት የአፍሪቃ ሰሜን ኮሪያ ናት።
|
ስዊድን የምትኖረዉ ኤርትራዊት ሜሮን እስጢፋኖስ ዛሬ ለዋለዉ የኤርትራ የነፃነት ቀን ደንታ የላትም።
|
በትግሪኛ የሐገር ነፃነት ማለት የሰዎች ነፃነት ማለትም ነዉ ትላለች የ ዓመቷ የመብት ተሟጋች።
|
በዚሕም ምክንያት ቀጠለች ሜሮን ዳንኤል ፔልስ እንደጠቀሰዉ ብዙ ሰዎች ማንም ሰዉ ነፃ ሳይወጣ የነፃነት ቀን የምናከብረዉ ለምድነዉ
|
የዛሬ ሃያ አምስት ዓመት የዛሬን ቀን የኤርትራ ነፃነት ሲታወጅ ርዕሠ ከተማ አስመራ በደስታ ፌስታ ፈንጠዝያ ተደበላልቃ ነበር።
|
ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በደስታ ባሕር ይዋኝ ለነበረዉ ሕዝባቸዉ ባደረጉት ንግግር ዛሬ የኤርትራ ዳግማዊ ልደት ነዉ።
|
አዲሲቱ ሐገር የመላዉ አፍሪቃ የልማት ዕድገት ተስፋ እንደምትሆንም የፕሬዝደንት ኢሳያስ መንግሥት ቃል ገብቶ ነበር።
|
ብሪታንያዊቱ የኤርትራ ጉዳይ አጥኚና ደራሲ ሚሼኤላ ሮንግ እንሚሉት ደግሞ በ አስመራን የጎበኙበት ወቅት ልዩ ጊዜ ነበር ።
|
ኤርትራ ከሙስና የፀዳች መንግሥቷ ለሁሉም ክፍት የፈለገዉ ሰዉ በፈለገ ጊዜ ሚንስትሩን ማናገር የሚችልባት ሐገር ነበረች።
|
በ ዎቹ ተሰደዉ የነበሩ ኤርትራዉያን በብዛት ወደ ሐገራቸዉ እየተመለሱ መዋዕለ ንዋያቸዉን ሥራ ላይ እያዋሉ ነበር።
|
ኢትዮጵያን ከኤርትራ ጋር የሚያዋስነዉ ድንበር በቅጡ ባለመካለሉ በ ሌላ ጦርነት ፈነዳ።
|
ኢሳያስ የቀድሞ ሚንስትሮች እና ታጋዮችን ሳይቀር የሚተቿቸዉን ሁሉ ባንድ ጊዜ እስር ቤት ወረወሯቸዉ ደራሲ ሮንጎ እንዳሉት።
|
ዲፕሎማቶች ሳይቀሩ ከአስመራ ዉጪ መንቀሳቀስ የሚችሉት መንግሥትን አስፈቅደዉ ነዉ።
|
የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የኤርትራ ጉዳይ ልዩ አጥኚ ሺይላ ኬታሩት የሰብአዊ መብት ጥሰቱ አሳሳቢ ነዉ።
|
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የዛሬ ሁለት ዓመት የኤርትራ መንግሥትን ሰዎችን በባርነት በማሰቃየት በመድፈር እና ማንገላታት ተጠያቂ አድርጎታል።
|
ሰብአዊ መብት ከሚጣስባቸዉ እና ወጣቶችን ለስደት ከሚዳርጉ ምክንያቶች አንዱ ብሔራዊ አገልግሎት ነዉ።
|
በትወራ ደረጃ ዓመት የሞላዉ ኤርትራዊ ለተወሰነ ጊዜ ወታደራዊ እና ሌሎች አገልግሎቶች የሚሰጥበት ግዳጅ ነዉ።
|
ብዙዎች ግን ለመንግሥት ገደብ የለሽ አገልግሎት የሚሰጥበት ነዉ ባዮች ናቸዉ።
|
ኤርትራ ዉስጥ ምርጫ ላለመደረጉም ከኢትዮጵያ ጋር ያለዉ ግጭት መፍትሔ አለማግኘቱን ተጠያቂ ያደርጋሉ።
|
የኤርትራ ስደተኞች ቁጥር እየተበራከተ ከመጣ ወዲሕ ጀርመንን ጨምሮ ጥቂት ምዕራባዉያን መንግሥታት ከአስመራ ጋር ያላቸዉን ግንኙነት ለማሻሻል አንዳድ እንቅስቃሴዎችን ጀምረዋል።
|
በ የቀድሞዉ የጀርመን የልማት ሚንስትር ጌርድ ሙለር አስመራን ሲገበኙ ባመቱ አንድ የኤርትራ ከፍተኛ የባለሥልጣናት ቡድን በርሊንን ጎብኝቷል።
|
ይላሉ አንዳድ መንግሥታት እና ዓለም አቀፍ ተዋኞች ከኤርትራ መንግሥት ጋር ለመገናኘት ጥሪት እያፈሰሱ ነዉ።
|
ከኤርትራ ጋር ያላቸዉን ግንኙነት ወደነበረበት ለመመለስ ባለፉት ሰወስት ዓመታት እየጣሩ ነዉ።
|
ከዚሕ ቀደም ያነሳሁት መሠረታዊዉ የሰብአዊ መብት ይዞታ በተጨባጭ ምን መሻሻል ተገኝቷል
|
ከቅርብ ዓመታት ወዲሕ ሥለ ፕሬዝደንት ኢሳያስ ጤና ማጣት የሚናፈሰዉ አሉባልታ እየተደጋገመ ነዉ።
|
ሰዉዬዉ አንድ ቀን አንድ ነገር ቢሆኑ ምናልባት ለዉጥ ሊመጣ ይቻላል ባዮች አሉ።
|
ደራሲ ሮንግ ግን ሥልጣኑ ከብዙዎቹ የኢሳያስ ጄኔራሎች ካንዱ እጅ አያመልጥም ባይ ናቸዉ ደራሲዋ።
|
ብሔራዊ ሸንጎዉ እና የፍትሕ ሥርዓቱን የመሳሰሉ ተቋማት ትክክለኛ ሥልጣን የላቸዉም።
|
ሥለዚሕ ኢሳያስ አፈወርቂ ጡረታ ቢወጡ ወይም ቢሞቱ ብዙ ጄኔራሎች አሉ።
|
ከነሱ በታች ደግሞ የወጣቱን ስሜት የሚጋሩ ወጣት የጦር መኮንኖች አሉ።
|
ዴሞክራሲያዊ መንግሥት ለመመስረት የሚደረግ እንቅስቃሴ ይኖራል ብዩ ግን አላምንም።
|
እንደ ሚመስለኝ አንዱ ጄኔራል ሥልጣኑን ከኢሳያስ የመዉረስ እድሉ ሰፊ ነዉ።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.