input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ከዚያም አንድ ግቢ ውስጥ አስገቡን ያለው ታሪኩ ኹኔታውን ያብራራል።
|
ግቢ ውስጥ እንደገባን ከመኪናው ላይ እየጉተቱ ካወረዱን በኋላ የያዝነውን ዕቃ ፊት ለፊት እንድናስቀምጥ ካደረጉን በኋላ በየተራ እያስቆሙ እያመናጨቁ ፈተሹን።
|
ወንዶችን ለብቻ ሴቶችንም ለብቻ ካደረጉን በኋላ የመጡት ወታደሮች ሁሉ ከ ጊዜ በላይ ቆጠሩን።
|
ወደ ፊታችን ሁለት ሰዎች መተው ቆሙ አንደኛው የእጅ ሽጉጥ የያዘ ሲሆን ሁለተኛው ሽመል ይዟል።
|
ባለመሣሪያው የአካባቢው የፀጥታ ክፍል ኃላፊ ሲሆን ባለሽመሉ የፖሊስ ኮሚሽን ነው።
|
ሁለቱ ሰዎች ወደኛ እንደቀረቡ ወታደሮቹም ዙሪያችንን ከበው እጃቸውን የመሣሪያቸው መላጭ ላይ አደረጉ በማለት ይቀጥላል የታሪኩ ጽሑፍ።
|
ወደ አካባቢው ዘመን ድራማን ለመሥራት ሲሄዱም ለ ኛ ጊዜያቸው እንደነበር ጽፏል።
|
ምክንያቱም ይላል ታሪኩ ምክንያቱም ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃ ማሪያም ደሳለኝ ስለነበሩ ነው።
|
እኛም ከጠቅላይ ሚኒስቴሩ ካሉበት ኬ ሜ እርቀት ላይ ነበርን።
|
ዳሩ መንግሥት የመንግስት ብቻ እንደሆነ ህዝብም ህዝብ እንደሆነ በአንድ ሀገር ሳንተያይ መኖር ከጀምርን አመት አልፎናል ሲልም ጽሑፉን አጠቃሏል።
|
የዳዊት ጽሑፍ፦ የዘመን ድራማ ፕሮዲውሰሮች በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ለምን ችግር ገጠማቸው
|
የቡድኑ አባላት ወደ ክልሉ ለቀረጻ የገቡት ከክልሉ መንግሥት እውቅና ውጪ በድብቅ ነው ብሏል ዳዊት።
|
ዳዊት ከአካባቢው የጸጥታ ኃላፊ አገኘሁት ባለው መረጃ የ ዘመን ድራማ ፕሮዲውሰሮች ውጭ ከሚገኝ ድርጅት ጋር ግንኙነት አድርገዋል ይላል።
|
ዳዊት በጽሑፉ ማጠቃለያ ላይ ባሰፈረው ዐረፍተ ነገር ግን ከላይ የገለጠውን የራሱን ክስ የሚቃረን ጽሑፍ ጽፏል።
|
ሳያስፈቅዱ ለቀረጻ መግባታቸው ብቻውን ከጥርጣሬ በዘለለ የውጭ ኃይል ተባባሪ ናቸው ብሎ ለመደምደም አያበቃም በሚል።
|
ድርቅ የሚያጠቃው የሽንሌ ዞን ከፊል ገጽታ የ ዘመን ድራማ ደራሲ መስፍን ጌታቸው ለዳዊት አጭር መልእክት በፌስቡክ አስፍሯል።
|
ስህተት በመሠራቱም በአግባቡ ይቅርታ ተጠይቀን ነው የተለቀቅነው ይላል መስፍን አክሎም ከዛ በኋላም እስካሁን ድረስ ሥራችንን በስፍራው እየሠራን እንገኛለን ብሏል።
|
ሽንሌ ከድሬዳዋ በ ኪ ሜ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ከተማ ነች።
|
ሁሌም ቢሆን ለእውነት ዋጋ መስጠት ትልቅነት ነው ሲል አጠቃሏል።
|
ይኽ በ ዘመን ድራማ ሠራተኞች ላይ ደረሰ የተባለውን እንግልት የሚገልጸዉን መረጃ በርካቶች በማኅበራዊ መገናኛ አውታሮች ተቀባብለውታል።
|
ጣና ሐይቅ ካለፉት አራት እና አምስት ዓመታት አንስቶ በመጤ አረም የመወረሩ ዜና በርካቶችን አስደንግጧል።
|
አረሙ በአፋጣኝ ካልተወገደ በዓባይ ምንጭነቱ የሚታወቀው የጣና ሐይቅን ሊያደርቀው ይችላል ተብሏል።
|
ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ዶይቸ ቬለ ከዘገበበት በኋላ የበለጠ ትኩረት ሊያገኝ እንደቻለ አንዳንድ አድማጮቻችን ገልጠውልናል።
|
የሀገራችን ህዝብ ተቆርቋሪነቱን በተለያየ ማኅበራዊ ድረ ገፅ እየገለፀ ይገኛል በማለት ይጀምርና መፍትኄ የሚለውንም ሐሳብ አስፍሯል።
|
ጣናን የወረረው እምቦጭ የተሰኘው መጤ አረም በኔ አስተሳሰብ ይህን አረም ለማጥፋት የክልሉ መንግሥት ከአቅሙ በላይ የሚሆን አይመስለኝም።
|
አረሙን ለማጥፋት ይረዳል በሚል የመፍትኄ ሐሳብ የሰጠን ሌላው የፌስቡክ ተከታታያችን የዑራኤል ልጅ ነኝ የሚል የፌስቡክ መጠሪያ አለው።
|
እንዲህ ይላል፦ ይህን አረም ለማጥፋት እንደ ሌሎች አገራዊ ጉዳዮች በቴሌ በኩል ገንዘብ የሚሠበሠብበት መንገድ ቢመቻች መልካም ነዉ።
|
ይሄነው ላቀው በበኩሉ፦ ጣናን ሐይቅ ፌደራሉ መንግሥት አይመለከተውም እንዴ
|
ሕዳሴ ግድብ መለመኛ ሆኗል በጣናም ይለመና ሲል ጣና ሐይቅ እንደ ሕዳሴው ግድብ በመንግሥት በኩል ትኩረት አልተሰጠዉም የሚል አስተያየቱን ሰጥቷል።
|
ኧረ ያገሬ ሕዝብ እንነሳ እንነጋገርበት ሌላ ሀገር አለን ወይ
|
ጣና ከሌለ ባሕር ዳር እሚባል ነገር ተረት ይሆናል ብሏል።
|
ታደሰ ወልደአብ በአጭር አረፍተ ነገር ያሰፈረው መልእክቱ፦ ይህን ያኽል ጊዜ ለምን ዝም ተባለ
|
ገበሬዎች በሐይቁ ዙሪያ እምቦጭ የተባለውን አረም ሲነቅሉ የሚያሳዩ ፎቶዎችም በማኅበራዊ መገናኛ አውታሮች ይገኛሉ።
|
ከፎቶዉ ጋር አረሙን ለማጥፋት አስቸኳይ መፍትኄ እንደሚያሻው የሚጠቁሙ መልእክቶችም ይነበባሉ።
|
ስፖርት ስፖርት መጋቢት ቀን ዓ ም የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ለጃፓኑ የኦሎምፒክ ውድድር ለመሳተፍ በድል ጎዳና እየገሰገሱ ነው።
|
ዩጋንዳን በደርሶ መልስ ለ የረቱት ሉሲዎቹ ከምዕራብ አፍሪቃዊቷ ካሜሩን ጠንካራ ተፎካካሪዎች ጋር ይፋለማሉ።
|
ሣምንታዊ የስፖርት ዘገባ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ለጃፓኑ የኦሎምፒክ ውድድር ለመሳተፍ በድል ጎዳና እየገሰገሱ ነው።
|
የእንግሊዙ ማንቸስተር ሲቲ በኤፍ ኤ ካፕ ድሉ ማግስት ለሻምፒዮንስ ሊግ ወሳኝ ፍልሚያ ራሱን እያዘጋጀ ነው።
|
በፕሬሚየር ሊጉ ዋነኛ ተፎካካሪው ሊቨርፑልም ነገ ምሽት በተመሳሳይ ሰአት ለሻምፒዮንስ ሊግ ሩብ ፍጻሜ ወሳኝ ጨዋታውን ያከናውናል።
|
በጁጂትሱ የትግል ስፖርት ኢትዮጵያውያን ተፋላሚዎች ለመጀመሪያ ጊዜ አራት ሜዳሊያዎችን አስገኝተዋል።
|
በአፍሪቃ የመረብ ኳስ ጨዋታ ከኢትዮጵያ ሁለት ቡድኖች ተካፋይ ኾነውዋል።
|
ሌላኛው የእንግሊዝ ቡድን ሊቨርፑል ከፖርቹጋሉ ፖርቶ ቡድን ጋር ነገ ምሽት በተመሳሳይ ሰአት ለሩብ ፍጻሜ ይጫወታል።
|
በፕሬሚየር ሊጉ ሊቨርፑል አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ማንቸስተር ሲቲን በኹለት ነጥብ በልጦ ይገኛል ነጥብ ሰብስቧል።
|
ባየር ሙይንሽን ዶርትሙንድን የጎል ጎተራ ባደረገበት ጨዋታ ያሸነፈው ለ ነበር።
|
ባለፉት ተከታታይ አምስት ጨዋታዎች ኹለት ጊዜ ሽንፈት የገጠመው ቦሩስያ ዶርትሙንድ ነጥብ አለው።
|
የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ከአንድ ዓመት በኋላ በጃፓን በሚካሄደው የበጋ ኦሎምፒክ ውድድር ተካፋይ ለመኾን የመጀመሪያ ደረጃ ማጣሪያውን አልፏል።
|
ቡድኑ አሁን በኹለተኛው ዙር የማጣሪያ ውድድር የሚገጥመው የካሜሩንን ቡድን ነው።
|
በካምፓላ ከተማ ፊሊፕ ኦሞንዲ ስታዲየም ውስጥ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረችው ለብሔራዊ ቡድኑ በአጥቂ መስመር ተሰላፊዋ የኾነችው ሎዛ አበራን በስልክ አነጋግረናታል።
|
ብሔራዊ ቡድኑ ለድል የበቃው ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች በመላ ተቋቁሞ እንደኾነ ተናግራለች።
|
ሌላው ባሳለፍነው ሳምንት ለኢትዮጵያውያን ስፖርተኞች ደማቅ ድል ኾኖ የተመዘገበው ኢትዮጵያውያን ተፋላሚዎች በአፍሪቃ የጁጂትሱ ትግል ስፖርት አራት ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸው ነው።
|
ያሬድ ቪዬና ኦስትሪያ ፖላንድ እንዲሁም ዱስልዶርፍ ጀርመንን በመሳሰሉ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ልምድ ያካበተ አትሌት ነው።
|
በሴት ተወዳዳሪዎች ዘርፍ ደግሞ መስከረም ዓለማየሁ ነጋሽ በኹለት የውድድር ዘርፎች የብር እና የነሐስ ሜዳሊያዎች አስገኝታለች።
|
የወርቁም ኾነ የብር ሜዳሊያው በኢትዮጵያ የጁጂትሱ ስፖርት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘ መኾኑ ተገልጧል።
|
የሞሮኮ ፌዴሬሽን እና ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽን የኢትዮጵያውያኑን አትሌቶች የመጓጓዣ የመኝታ እና ሌሎች ወጪዎችን እንደሸፈኑ ተገልጧል።
|
ላለፉት ሁለት ሳምንታት በመቐለ ሲካሄድ የሰነበተው ኛው የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች የስፖርት ሻምፒዮና ባሳለፍነው ቅዳሜ ተጠናቋል።
|
የውድድሩ አዘጋጆች እንደገለፁት በተለይም በኦሎምፒክና እግርኳስ ስፖርቶች በርካታ ተስፋ የሚጣልባቸው ተማሪ ስፖርተኞች በውድድሩ መታየታቸው ተገልጧል።
|
በኦሎምፒክ ውድድሮች ኦሮምያ ክልል የወርቅ ሜዳልያዎች በማግኘት ውድድሩን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ አማራ ክልል ትግራይ ወርቅ ሜዳልያዎች በማግኘት ተከታታይ ደረጃዎች ይዘዋል።
|
በፓራ ኦሎምፒክ ስፖርቶች ኦሮምያ በአጠቃላይ ሜዳልያዎች በማግኘት የበላይ ሲሆን አማራ ትግራይ ሜዳልያዎች በማስመዝገብ ተከታትለው ውድድሩ ጨርሰዋል።
|
ሌላው ስፖርተኛ ተማሪዎቹ የተሳተፉበት ውድድር የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ናቸው።
|
በዚሁ ውድድር የአማራ ክልል ባህል ስፖርት ተወዳዳሪዎች ወርቅ ሜዳልያ በማስመዝገብ ቀዳሚ ሆነው ያጠናቀቁ ሲሆን ትግራይና አዲስ አበባ ተከታዮቹ ደረጃዎች ይዘዋል።
|
በመዝግያው ዕለት በተካሄደው የወንዶች እግርኳስ ፍፃሜ ኦሮምያ ደቡብ ክልልን አንድ ለባዶ በመርታት አሸናፊ ኾኗል።
|
በአጠቃላይ ኦሮምያ የውድድሩ አጠቃላይ አሸናፊ ሲሆን አማራ ሁለተኛ ትግራይ ሶስተኛ በመሆን ውድድራቸው አጠናቀዋል።
|
በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች የስፖርት ሻምፒዮና በርካታ ተተኪ ስፖርተኞች የሚፈሩበት መኾኑን አዘጋጆቹ ለዶይቸ ቬለ ገልፀዋል።
|
ትናንት ይፋ የሆነዉ ፕሮጄክት ከሁለቱ ዞኖች ተፈናቅለዉ ለነበሩ ከ ሺሕ የሚበልጡ ነዋሪዎችን ይረዳል።
|
ታድያ የወጣትነት ጊዜ ሲደርስ ለዚህ መሰረት የሆነውን የትምህርት ዘርፍ ለመከታተል ወይም ጨርሶ በሌላ መስክ ለመሰማራት እንወስናለን።
|
ወደሚፈልጉት የሙያ ዘርፍ ለመግባት የተለያዩ ነገሮች ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ።
|
አንዳንዶች የበፊቱ ምኞታቸው አሁን ካለው ጋር ፍፁም ተቃራኒ ሆኖ ሲያገኙ ሌሎች ደግሞ በዚሁ የሙያ መስክ ገፍተው የስራውን ዓለም ይቀላቀላሉ።
|
የ አመቷ መክሊት መርሻ ከሁለት ዓመት በፊት በማህበራዊ ሳይንስ ወይም ሶሲዮሎጂ በከፍተኛ ደረጃ ትምህርት አጠናቃለች።
|
መክሊት ዛሬ ለሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር መፅሄቶች ለማስተዋወቂያ የሚሆኑ ፎቶዎች እያነሳች ትሸጣለች።
|
ወጣቷ መሆን የምትፈልገውን ወይንም አቅጣጫዋን አስቀድማ ብታውቅም በወቅቱ በምርጫዋ ብዙዎች እንደማይረኩ ታውቅ ነበር።
|
የስራ ቦታ ሆኖ ስለ ዕረፍት ወይም ሌላ ስራ ማለም ሌላው ያነጋገርነው በንቲ እጄታን ነው።
|
ይሁንና በንቲ ዛሬ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና ሬዲዮ ድርጅት እየሰራ አይደለም መስሪያ ቤት ቀይሯል።
|
በዚህም ፍላጎት ላይ ተመርኩዟ ይህንን ዕውን ለማድረግ እየሰራች ትገኛለች።
|
እነዚህ ነገሮች ምርጫዬ ትክክል እንደነበርና ነኝ ያልኩትን ለመሆኔ ማሳያ ሆነውኛል ትላለች ምስራቅ እዚህ እስክትደርስ የነበረውን ውጣ ውረድ እያስታወሰች።
|
ወጣቶች በተመኙት የስራ መስክ ለመሰማራት ስለሚያደርጉት ትግል በዛሬው የወጣቶች ዓለም የቃኘነው ርዕስ ነው።
|
ሣምንታዊ የስፖርት ዘገባ ጥቅምት አምስት ቀን ዓም ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ቢስማርክ የጉባኤዉ መሐንዲስ ብዙ ጊዜ በታሪክ ለሚፈፀሙ በደሎች የገንዘብ ካሳ ይከፈላል።
|
ዝክሩ መነሻ ጉባኤ ዉጤቱ ማጣቃሻ የዛሬ አስተጋብቶ መድረሻችን ነዉ ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
|
አፄ ምኒሊክ የመሩት ኢትዮጵያዊ ሐገር ነፃነቱን ለማስከበር የከፈለዉ መስዋዕትነት፥
|
በኢጣሊያ ቅኝ ገዢዎች ላይ የተቀዳጃዉ ድል ለኢትዮጵያዊዉ ክብር አኩሪ ታሪክነቱ፥
|
ለድፍን ጥቁር ሕዝብ የነፃነት እኩልነቱ አብነት አለኝታነቱ በርግጥ የዘመን ሒደት ሊሽረዉ አይችልም።
|
ትግሉ ፀረ ቅኝ አገዛዝ አላማ ግቡ ነፃነት እኩልነት መሆኑ አያነጋግርም።
|
አክራ ዳሬ ሰላም ወይም ሌላ ከመሆን ይልቅ በርሊን መሆኑ ነዉ የዛሬዉ ዚቅ።
|
ከሕዳር አስራ አምስት እስከ እስከ የካቲት አጋማሽ የዘለቀዉ ጉባኤ ከተሰየመበት አዳራሽ አጠገብ አንዲት የመታሰቢያ ሰሌዳ ቆማለች።
|
ሰሌዳዉን ያቆመዉ የቶጎዉ ተወላጅ ቪክቶር ድሲድሶኑ የያኔዉን ታሪክ አፍሪቃዉን የመዘንጋት የለባቸዉም ባይ ነዉ።
|
ዛሬ እዚያ ያለዉን ችግር ያኔ ከተፈፀመዉ ጋር ማገናኘት ሥለምሻ ነዉ።
|
ይሕ ሰሌዳ በቅኝ አገዛዝ ዘመን የተፈፀመዉ በደል እንዳይረሳ ማስታወሻ እንዲሆን እፈልጋለሁ።
|
ለዚሕም ነዉ ያኔ አፍሪቃ በተቀራመቱባት ሥፍራ መቆም አለበት ብዬ ያሰብኩት።
|
ኢጣሊያ ከኦስትሪያ ሐንጋሪ እና ከጀርመን ጋር የጦር ቃል ኪዳን ስትፈራረም፥
|
በተለይ ፈረንሳይ የሊዮፖልድን እርምጃ ደግፋለች መባሉ በጣሙን የፖርቱጋልና የብሪታንያን ቁጣ ቀስቅሶ ነበር።
|
ኮንጎ በሊዮፖልድ ዳግማዊ እጅ መዉደቋና በዚያ በኩል የሚደረገዉ የሸቀጥ ዝዉዉር መታገዱ ለቢስማርክና ለሌሎቹ አሳሳቢ ነበር።
|
ሌሎች ሐያል መንግሥታትም ወደ ኮንጎ የመግባት መብታቸዉ መጠበቅ አለበት የሚል ነበር።
|
የእርስበራሳቸዉ መፈራራት ምክንያት ከሁሉም በላይ አፍሪቃን የመቀራመቱ ፍላጎት መሠረት ሆኖ ቢስማርክ ያን ጉባኤ ጠሩ።
|
ሐያሉ የአፍሪቃን ካርታ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠዉ አፍሪቃን ሲቀራመቱ ሴለር እንደሚሉት አንድም አፍሪቃዊ አልተወከለም ነበር።
|
በግልፅ መታወቅ ያለበት አንድም አፍሪቃዊ በዚያ ጉባኤ እንዲገኝ አልተጋበዘም ነበር።
|
ያኔ አይደለም ዛሬም የዚያን ዘመኑን ታሪክ የሚያስብ አፍሪቃዊ መሪ የለም ካለም አይታወቅም።
|
ዉሉ ኢትዮጵያ የምፅዋን የመሳሰሉ ወደቦች ጉባኤዉ ሪታንያ እዉቅና የሰጠችበት ነዉ።
|
የሐይል ሚዛንን አሰላለፍ እልፍ ሲልም የዘር ወገን ቅርበት በሚዘዉረዉ የፖለቲካ ጨዋታ ሐቅ እዉነት፥
|
የበርሊኑ ጉባኤ ልዩነት ድብልቅልቁ ወጥቶ አንደኛና ሁለተኛ በሚባሉት ጦርነቶች አለም እስክትነድ ድረስ የድፍን አፍሪቃ ሕዝብ በቅኝ ገዢዎች ሐይላት ተጨፍጭፏል።
|
ዉይይት ላይ ከሚካአሉት አፍሪቃዉያን አንዱ ስቬን ሜካሪደስ እንደሚለዉ በቅኝ አገዛዝ ዘመን በአፍሪቃዉያን ላይ ለተፈፀመዉ በደል ካሳ የማይከፈልበት ምክንያት አይገባዉም።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.