query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
1
300
passage
stringlengths
78
13.7k
category
stringclasses
7 values
link
stringlengths
28
740
⌀
source_dataset
stringclasses
3 values
3c330a7bfc24bc605e27489fdcbf2696
3d6e82ca1eec9d7667dc052925ff1619
ዑስታዝ አቡበከር አህመድ ለሁለተኛ ጊዜ የዕለት ፍጆታና የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ፡፡
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 26/2012 ዓ.ም (አብመድ) ዑስታዝ አቡበከር አሕመድ ለበደቡብ ወሎ ዞን እና ደሴ ከተማ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ተፅዕኖን ለመቀነስ የሚረዳ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የዕለት ፈጆታ ምግብና የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ድጋፉ በዑስታዝ አቡበከር አህመድ በኩል ሲደረግ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከተማ አስተዳደሩና ዞኑ የተደረገው ድጋፍ ሌሎችን የሚያነሳሳ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡የኮሮና ቨይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖዎችን እያሳረፈ ይገኛል፡፡ በዚህ ወቅት የማኅበረሰቡና የበጎ አድራጊዎች የግልና የቡድን መረዳዳቶች የሕይወትን ተስፋ ለነገ በማሻገር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው፡፡ዑስታዝ አቡበከር አህመድ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ለዜጎች ድጋፍ ከሚያርጉ በጎ አድራጊዎች መካከል ናቸው፡፡ ከዚህ በፊት ደሴ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በደቡብ ወሎ ዞን ለሚገኙ ችግረኞች የዕለት የምግብ ፍጆታ የሚውል ድጋፍ በተወካያቸው አማካኝነት አስረክበው ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ በአካል በመገኘት ለደሴና ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደሮችና ለደቡብ ወሎ ዞን አንድ ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ለሁለት ሺህ ሰዎች ዱቀት፣ ዘይትና ሩዝ ለሕክምና ሙያተኞች የሚያገለግል የኬሚካል መርጫ መሣሪያ፣ ልብስ፣ ቦቲ ጫማና የሙቀት መለኪያ አስረክበዋል፡፡‘‘ያለሃይማኖት፣ ፖለቲካና አካባቢያዊ ልዩነት የተቸገሩ ዜጎችን የምንታደግበት ወቅት ነው’’ ያሉት ዑስታዝ አቡበከር ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል፡፡ዑስታዝ አቡበከር ያከናወኑት በጎ ተግባር ለሌሎች ትልቅ ትምህርትና መልእክት መሆኑን የተናገሩት የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሰይድ መሐመድ የኢኮኖሚ ተፅዕኖውን ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%91%e1%88%b5%e1%89%b3%e1%8b%9d-%e1%8a%a0%e1%89%a1%e1%89%a0%e1%8a%a8%e1%88%ad-%e1%8a%a0%e1%88%85%e1%88%98%e1%8b%b5-%e1%88%88%e1%88%81%e1%88%88%e1%89%b0%e1%8a%9b-%e1%8c%8a%e1%8b%9c-%e1%8b%a8/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
5e128a8a5bb17c2bddfa8d5b674bc54e
470b5a411ada1c7d8860200a2d094800
ሠራዊቱ መቀሌ ከተማን ለመቆጣጠር መቃረቡን አስታወቀ
ለአፍሪካ ኅብረት ልዩ ልዑካን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ተሰጠየአገር መከላከያ ሠራዊት በተለያዩ አቅጣጫዎች ማጥቃት ሰንዝሮ በርካታ አካባቢዎችን ካስለቀቀ በኋላ፣ የመቀሌ ከተማን በቀናት ውስጥ ለመቆጣጠር ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን መያዙን አስታወቀ፡፡የመከላከያ ሠራዊት ኅብረት ሥልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተና ጄኔራል ሀሰን ኢብራሂም ዓርብ ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት በሰጡት መግለጫ፣ የመከላከያ ሰራዊት ሀውዜን፣ አልነጃሺ፣ አዲቀየህ፣ ማይመሳኖንና ውቅሮን ከሕወሓት ታጣቂ ኃይል ሙሉ በሙሉ ነፃ ማድረጉን አረጋግጠዋል።የሕግ ማስከበር ዘመቻው በውጤታማነት መከናወኑን ያስታወቁት ጄኔራል መኮንኑ በዓድዋ ግንባር የተንቀሳቀሰው ሠራዊት ሀውዜንን፣ አብርሃ ወአፅብሃንና ውቅሮን የተቆጣጠረ መሆኑን፣ አጉላን ደግሞ በግማሽ ቀን መያዙን ገልጸዋል። ይኼው ኃይል በመቀሌ አቅራቢያ የሚገኘውን መሰቦ ተራራ ለመያዝ እየገሰገሰ እንደነበርና ከተማዋን በጥቂት ቀናት ውስጥ ለመቆጣጠር እንደሚችል ተናግረዋል።በሁለተኛው ግንባር ማለትም በአዲግራት በኩል ሠራዊቱ ሰንቀጣንና አል ነጃሺን በመቆጣጠር ውቅሮን መያዙን በመግለጫው አስረድተዋል።በሦስተኛው የራያ ግንባር የሚገኘው ሠራዊት አዲቀይህን ከያዘ በኋላ ሔዋነን በመቆጣጠር የትግራይ ልዩ ኃይልን ሁሉንም ምሽጎች ደርምሶ ወደፊት መገስገሱን አስታውቀዋል። በአጉላን በኩል መንገድ ለመዝጋት ቢሞክርም እንዳልተሳካለትና ወደኋላ ማፈግፈጉን ጠቁመው፣ አሁን ግን መቀሌ ከተማ ብቻ መቅረቱንና በጥቂት ቀናት ወስጥ ዘመቻው እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል፡፡የሦስተኛው ምዕራፍ ዘመቻ ዓላማ የሕወሓት አመራሮችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ለሕግ ማቅረብ መሆኑን ያስታወሱት ሌተና ጄኔራል ሀሰን፣ ሠራዊቱ ነፃ ባወጣባቸው ሥፍራዎች ሁሉ የትግራይ ሕዝብ በሠራዊቱ ላይ አልተኮሰም ብለዋል፡፡ ይህም የሕወሓት አመራሮችና ሕዝቡ አንድ አለመሆናቸውን ማረጋገጫ ነው ሲሉ አክለው፣ ሕዝቡ እንዲያውም ለሠራዊቱ ወገንተኝነት አሳይቷል ሲሉ ሁኔታውን አስረድተዋል፡፡የሕወሓት አመራሮችና ቡድናቸው በፕሮፓጋንዳ ጭምር እያፈገፈጉ መሄዳቸው ሽንፈታቸውን እያረጋገጠ እንደሆነም ጄኔራል ሀሰን ጠቁመዋል።የደቡብ ግንባር የበላይ አዛዥ ሌተና ጄኔራል ባጫ ደበሌ ከሥፍራው በሰጡት ሌላ መግለጫ፣ ከባድ ምት ያረፈበት የትግራይ ልዩ ወደ አዲጉደም እንደሸሸ አስረድተዋል፡፡ ሠራዊቱ አካባቢውን በተቆጣጠረበት ወቅት ልዩ ኃይሉ ይጠቀምባቸው የነበሩ ስድስት ታንኮች፣ ሁለት ዙ23 የአየር መቃወሚያዎችና በርካታ መሣሪያዎች መደምሰሳቸውን አስታውቀዋል፡፡ ሠራዊቱ አስቸጋሪ መልክዓ ምድር በብቃት በማለፍ ከፊቱ የቆመውን ኃይል መደምሰሱን አስረድተዋል፡፡ይህ በዚህ እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መንግሥታቸው በሕወሓት አመራር ከሁለት ዓመት በላይ ሲከናወኑ የቆዩትን ፀብ አጫሪነትና አገር የማፍረስ እንቅስቃሴዎች በከፍተኛ ሆደ ሰፊነትና ትዕግሥት ማሳለፉን፣ ለበርካታ ጊዜያትም ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መድከሙን፣ ነገር ግን ይህም አልበቃ ብሎ በሰሜን ዕዝ የአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የተፈጸመው ጥቃት በአገሪቱ ሕግ መሠረት ከፍተኛ የአገር ክህደት ወንጀል በመሆኑ ሕገ መንግሥታዊውን ሥርዓት ለማስከበር ኃላፊነቱ እንደሆነ አስታወቁ፡፡ ዓርብ ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበርና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ልዩ ልዑክ ተቀብለው ሲያነጋግሩ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት፡፡ የላይቤሪያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ኢሊየን ጆንሰን ሲሪሊፍ፣ የሞዛምቢክ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጆአኪም ቺሳኖ፣ እንዲህም የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ካግሌማ ሞቴላንተ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በትግራይ ክልል እየተካሄደ ባለው ዘመቻ ላይ ለመነጋገር አዲስ አበባ የመጡት፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ‹‹ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ›› በሚለው መርህ መሠረት ልዩ ልዑኩን በመላካቸውና አንጋፋዎቹ የልዑካን አባላትም ሥጋት ገብቷቸው እዚህ ድረስ በመምጣታቸው አመሥግነው፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ መንግሥቱ የተሰጠውን ሕግ የማስከበር ኃላፊነት እየተወጣ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ይህንን ኃላፊነት አለመወጣት ግን ኢትዮጵያን ትልቅ ዋጋ ያስከፍላታል ሲሉ ማስታወቃቸውን፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ካወጣው መግለጫ መረዳት ተችሏል፡፡
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/20602
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
2856e8185cba3fafd8217d689466abc7
61629f12ced148f48609c4e32bc03fbc
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን 49 ቀበሌዎች በኦሮሚያ ስር እንዲተዳደሩ መካለላቸውን የክልሉ መንግስት አስታወቀ
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን 49 ቀበሌዎች በኦሮሚያ ክልል ስር እንዲካለሉ መደረጉን የክልሉ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።በኦሮሚያ እና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መሃል ሲስታዋል የነበረውን ችግር ለመፍታት የወሰን ማካለል ስራ እየተሰራ መሆኑንም የቢሮው ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ አስታውቀዋል።አቶ አዲሱ እንዳሉት በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለው የወሰን ችግር በተለያዩ ጊዜያት ግጭቶችን በማስከተል ለበርካታ ሰዎች ሞትና ለንብረት ውድመት ምክንያት ነበር።በ1997 የተደረገውን ህዝበ ውሳኔ መሰረት በማድረገግ ከወሰን ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱም ክልሎች ከስምምነት መድረሳቸውን ያስታወሱት ሃላፊው፤ በስምምነቱ መሰረት ወሰን የማካለሉ ስራን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።በዚህም መሰረት በምስራቅ ሀረርጌ ዞን እስካሁን በተከናወኑ ስራዎች በሁለቱም ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ ሲነሳባቸው ከነበሩ 68 ቀበሌዎች 48ቱ በኦሮሚያ ክልል ስር እንዲተዳደሩ የሚያደርግ የማካለል ስራ መጠናቀቁን አስታውቀዋል ።የ19 ቀበሌዎችን ወሰን የማካለሉ ስራ አሁንም ቀጥሏል ያሉት አቶ አዲሱ፤ ወሰን የማካለል ስራውም በቁንቢ ወረዳ 3 ቀበሌዎች፣ በአመዩ ወረዳ 4 ቀበሌዎች፣ በሚደጋ ቶላ ወረዳ 2 ቀበሌዎች፣ በጉርሱም ወረዳ 2 ቀበሌዎች፣ በጭናክሰን ወረዳ 2 ቀበሌዎች እንዲሁም በሜታ ወረዳ የሚገኝ 1 ቀበሌ ነው ብለዋል።ከወሰን ጋር ተያይዞ የሚስተዋለው ግጭት በ1997 ዓ.ም የተካሄደው ህዝበ ውሳኔ ላይ በመመርኮዝ ሰላማዊ እና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ በመፍታት ድንበር አካባቢ ያሉ አስተዳደሮች የግጭት እና የሰዎች ህይወት የሚያልፍባቸው ሳይሆን ሰላምና ልማት የሚረጋገጥበት እንዲሁም የህዝቦች ወንድማማችነት የሚመሰረትበት ስፍራ እንዲሆን የኦሮሚያ ክልል መንግስት በሰላም እና በብስለት እንዲሁም ሃላፊነት በተሞላበት መንገድ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።የኦሮሚያ ክልል መንግስት ከወሰን ጋር በተያያዘ ከክልሉ አዋሳኝ ከሆኑ ጎረቤት ክልሎች ጋር የሚነሱ ችግሮችን ሰላማዊ እና ህዝብን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ አዲሱ አረጋ አያይዘው ጠቁመዋል።በዚህ መልኩም ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል መካከል ከአስተዳደር ወሰን ጋር ተያይዞ ሲስተዋል የነበረ ችግር የወሰን ማካለል ስራ መጠናቀቁንም አስታውቀዋል።ከጋምቤላ፣ ከአማራ እና ከደቡብ ክልሎች ጋር ከወሰን ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችንም የክልሉ መንግስት ሰላማዊ በሆነ እና ህዝቡን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ ለመፍታት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አቶ አዲሱ አስታውቀዋል-(ኤፍ.ቢ.ሲ) ።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/29317/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
dae07ad2f46564999d1f4da09d784bf6
2917c1d94dc4b8e03ad786f86d719a8b
ጆ ባይደን ተቀማጩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕን በማሸነፍ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነው ተመርጠዋል።
የአፍሪካና የተቀረው ዓለም መሪዎች ለባይደን የደስታ መልዕክት እያላኩ ነው\nይህን ተከትሎ በርካቶች ደስታቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። በትላልቅ የአሜሪካ ከተሞች ያሉ የጆ ባይደን ደጋፊዎች አደባባይ ወጥተው ደስታቸውን እየገለፁ ነው። የትራምፕ ደጋፊዎች ደግሞ በተቃራኒው ተቃውሞ ላይ ናቸው። የጆ ባይደን መመረጥ ይፋ ከሆነ በኋላ በርካታ የዓለም መሪዎች ተመራጩን ፕሬዝደንት እንኳን ደስ አለዎ እያሉ ይገኛሉ። የኢትዮጵያው ጠ/ሚ አቢይ አሕመድ በትዊተር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት ጆ ባይደንን 'እንኳን ደስ አለዎ' በለዋለቸዋል። የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂም ለተመራጩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የእንኳን ደስ አለዎ መልዕክት እንደላኩ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል። የዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖምም ለጆ ባይደን መልካም ምኞት ልከዋል። 'ከአዲሱ አስረተዳደር ጋር አብረን ለመሥራት ዝግጁ ነን' የሚል ሐሳብም አክለዋል። ፕሬዝደንት ትራምፕ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ከዶ/ር ቴድሮስ ጋር እሰጥ አገባ እንደገቡና ሃገራቸውን ከዓለም ጤና ድርጅት ለማስወጣት መዛታቸው አይዘነጋም። የካናዳው ጠ/ሚ ጀስቲን ትሩዶ ቀደም ብለው የእንኳን ደስ አለዎ መልዕክት ካስተላለፉ መሪዎች መካከል ናቸው። የዚምባብዌው ፕሬዝደንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ፣ የዩጋንዳው ዩዌሪ ሙሴቪኒ፣ የኬንያው ኬንያታ፣ የጋናው አኩፎ አዶ የደስታ መልዕክታቸውን ለጆ ባይደን ከላኩ የአፍሪካ መሪዎች መካከል ናቸው። አብዛኛዎቹ መሪዎች ለአዲሱ የአሜሪካ ፕሬዝደንት የደስታ መልዕክት ከላኩ በኋላ ከአሜሪካ ጋር አብሮ ለመሥራት ዕቅድ እንዳላቸው አሳውቀዋል። ፕሬዝደንት ትራምፕ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎቻቸው ትችት ይደርስባቸዋል። ጆ ባይደን ማናቸው? ጆ ባይን የቀድሞ የፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ምክትል ፕሬዝደንት ሆነው አገልግለዋል። ባይደን የፖለቲካ ሕይወታቸው የጀመረው ከ47 ዓመታት በፊት ነበር። የአሜሪካ ፕሬዝደንት ለመሆኑን ጥረት ማድረግ የጀመሩት ደግሞ ከ33 ዓመታት በፊት እአአ 1987 ላይ። ጆ ባይደን ትራምፕ ያበላሹትን የውጭ ግንኙነት አስተካክላለሁ፤ አሜሪካ ያስቀየመቻቸውን ወዳጆቿን ልብ እጠግናለሁ ብለዋል። ከኢራንና ከቻይና ጋር የሚከተሉት ፖሊሲም ትራምፕ ጋር የሚቃረን ነው። ባይደን የአሜሪካን 2020 ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸው የተረጋገጠው ከ270 ኤሌክቶራል ድምጽ በላይ ማግኘታቸውን ተከትሎ ነው።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
3c6b6ad7bb83254a5f1a36f12ee2d26d
e042241a69bf5018515961039e4a57b5
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለማላዊና ለአስካይ አየር መንገዶች ኃላፊዎች ሾመ
አዲስ አበባ፤ መስከረም 26/2006 (ዋኢማ) – ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፣ የአየር መንገዱ ዋና የፋይናንስ ኦፊሰር አቶ ቃሲም ገረሱ በቅርቡ እንደ አዲስ ኩባንያ የተቋቋመውን የማላዊ አየር መንገድን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት እንዲመሩ ተሹመዋል፡፡ አቶ ቃሲም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የማኔጅመንት አባልነትና በከፍተኛ የፋይናንስ ባለሙያነት የረዥም ጊዜ ልምድ ያካበቱ ኃላፊ ናቸው፡፡ የማላዊ ብሔራዊ አየር መንገድ ‹‹ኤር ማላዊ›› በኪሳራ ከተዘጋ በኋላ የማላዊ መንግሥት አየር መንገዱን በማፍረስ ማላዊ ኤርላይንስ ሊሚትድ የተሰኘ አዲስ ኩባንያ መሥርቷል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ በተቋቋመው ኩባንያ ላይ የ49 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ ገዝቷል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 25 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስት ለማድረግና አንድ ቦይንግ 737 እና አንድ ቦምባርዲየር ‹‹ኪው›› 400 አውሮፕላኖችን ለማላዊ ኤርላይንስ ለማቅረብ ተስማምቷል፡፡ አየር መንገዱን የሚመራው ከኢትዮጵያ አየር መንገድና ከማላዊ ኤርላይንስ በተውጣጡ ባለሙያዎች እንደሆነ ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡የማላዊ አየር መንገድ ፈርሶ እንደ አዲስ የተቋቋመ ኩባንያ በመሆኑ፣ አቶ ቃሲም ከባድ ሥራ እንደሚጠብቃቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በተያያዘም በምዕራብ አፍሪካ የሚንቀሳቀሰው አስካይ አየር መንገድን እንዲመሩ አቶ ይስሃቅ ዘወልዲ ተመርጠዋል፡፡ አቶ ይስሃቅ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአሊያንስና የኮርፖሬት ስትራቴጂ ፕላኒንግ ምክትል ፕሬዚዳንት ነበሩ፡፡ አቶ ይስሃቅ በተለያዩ ኃላፊነቶች አየር መንገዱን ለረዥም ዓመታት ያገለገሉ ከፍተኛ የማኔጅመንት አባል ናቸው፡፡ የአስካይ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ለሦስት ዓመታት ያገለገሉት አቶ ቡሴራ አወል በአቶ ይስሃቅ የተተኩ ሲሆን፣ አቶ ቡሴራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቺፍ ኮሜርሺያል ኦፊሰር ሆነው ተሹመዋል፡፡ አስካይ አየር መንገድ እ.ኤ.አ. በ2008 መመሥረቱ ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ45 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ አለው፡፡ አየር መንገዱ ሥራውን የጀመረው እ.ኤ.አ. በ2010 ነው፡፡መቀመጫውን በሎሜ ቶጎ ያደረገው አስካይ በምዕራብና በመካከለኛው አፍሪካ 22 መዳረሻዎች ሲኖሩት፣ ሰባት አውሮፕላኖች አሉት፡፡ እንደማንኛውም ጀማሪ አየር መንገድ አትራፊ ያልነበረው አስካይ በአሁኑ ወቅት ትርፋማ መሆን እንደጀመረ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ለዚህም የአቶ ቡሴራ ማኔጅመንት ቡድን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ ምንጮች አስረድተዋል፡፡  (ምንጭ- ሪፖርተር)
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/28184/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3ea736ac20d6cd6c1d58445486c6fa8e
2fcb1501e98b988491cba3131c8f5e8d
የትምህርት ሚኒስቴርና የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና አመራሮችና ሰራተኞች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የደም ለገሱ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 14፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የትምህርት ሚኒስቴር እና የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አመራሮች እና ሰራተኞች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የደም ልገሳ መርሃ ግብር አካሂደዋል።የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አመራሮች እና ሰራተኞች “ደሜን ለህግ መከበር ህይወታቸውን ለሰጡት ለመከላከያ ሰራዊት አባላት” በሚል መሪ ቃል ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የደም ልገሳ እና የ3 ሚሊየን ብር ገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።በደም ልገሳ መርሃ ግበሩ ተገኝተው የተገኙት በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ የአስተዳደር ዘርፍ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቶ አድማሱ አንጎ፥  ለሀገር መከላከያ ስራዊት ደም መለገስ ብቻ ሳይሆን የተቋሙ አመራሮች፣ ሰራተኞች እና ተቋሙ 3 ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።በሀገር መከላከያ ስራዊት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ሕግ የማስከበር እና ሁሉም ሰው ከሕግ በታች መሆኑን ማሳያ ነው ሲሉም ተናግረዋል።አቶ አድማሱ አክለውም፥ በሀገሪቱ የተጀመረው የለውጥ ሂደት የሕግ የበላይነት የሚያረጋግጥ እና የዴሞክራሲ ሥርዓት በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለመገባት የሚያስችል በመሆኑ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ሂደት ሁሉ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እየተወጣ ያለና በቀጣይም ይህንን ተግባር አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።በተያያዘ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞችም “ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ክብር እቆማለሁ” በሚል መሪ ቃል በዛሬው እለት የደም ልገሳ አካሂደዋል።በደም ልገሳ ፕሮግራሙም ከሚኒስትሩ አመራሮች እና ሰራተኞች በተጨማሪ  የክልል እና ከተማ አስተዳደር የትምህርት  ቢሮ  አመራሮች እና ተወካዮችም ተሳትፈዋል።የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ገረመው ሁሉቃ በዚሁ ጊዜ፥ የደም ልገሳው መርሃ ግብሩ ዓላማ  የሀገርን ሰላም በማስጠበቅ ላይ ለተሰማራው የመከላከያ አለኝታን ለማሳየት ነው ብለዋል።በሀገሪቱ ሰላም እስኪረጋገጥ ድረስም የትምህርት ሚኒስቴር ለመከላከያ ሰራዊት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀዋል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%89%b5%e1%88%9d%e1%88%85%e1%88%ad%e1%89%b5-%e1%88%9a%e1%8a%92%e1%88%b5%e1%89%b4%e1%88%ad%e1%8a%93-%e1%8b%a8%e1%8c%a0%e1%89%85%e1%88%8b%e1%8b%ad-%e1%8b%90%e1%89%83%e1%89%a4-%e1%88%95/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b11973c6374bea746a007db0c9ff2378
df486b0c4b123ca4e24bc0f46648671c
ወላይታ ድቻ ጃኮ አረፋት እና አምረላህ ደልታታን አስፈርሟል
በዝውውር መስኮቱ የነቃ ተሳትፎ እያደረገ የሚገኘው ወላይታ ድቻ የሁለት ተጫዋቾችን ፊርማ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡ ጃኮ አራፋት እና አምራላ ደልታታም ለክለቡ የፈረሙ ተጫዋቾች ናቸው፡፡ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በመጀመሪው አመት ነጥረው ከወጡ ተጫዋቾች አንዱ የሆነው እና ለሀዋሳ ከተማ 12 የሊግ ግቦች በማስቆጠር ድንቅ አመት ያሳለፈው የቀድሞው የአንዚ ማካቻካላ እና ሲኤፍ ሞናና አጥቂ ስሙ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክለቦች እና የእስራኤል ፕሪምየር ሊግ ክለቡ የሆነው ሀፖኤል አክሬ ጋር ቢያያዝም ለእረፍት ካመራበት ሀገሩ በመምጣት በቃል ደረጃ ተስማምቶበት የነበረው ወላይታ ድቻን በአንድ አመት ውል መቀላቀሉ ታውቋል፡፡ሌላኛው የወላይታ ድቻ ፈራሚ የሆነው አምረላ ደልታታ ነው፡፡ በሀዲያ ሆሳዕና ጋር ሁለት የውድድር ዘመናትን ማሳለፍ የቻለው የቀኝ መስመር አማካዩ ሀዲያ ሆሳዕና ምንም እንኳን በዘንድሮው አመት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ባይቀላቀልም መልካም የውድድር አመት ማሳለፍ ችሏል፡፡ወላይታ ድቻ በዝውውር መስኮቱ ሁለቱን ጨምሮ በአጠቃላይ 9 ተጫዋቾችን ማስፈረም ችሏል፡፡
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/29912
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e45ee12c3dac400938f282a792248034
b426baa53c1988abc5b5ad1eac6cb92b
የጣሊያን የመጀመሪያው የኮቪድ-19 ታማሚ በፈረንጆቹ የካቲት 21 ሚላን አቅራቢያ ነበር ሪፖርት የተደረገው
አዲሱ የኮሮና ቫይረስና ኮቪድ 19 በፈረንጆቹ ከመስከረም 2019 ጀምሮ በጣሊያን ውስጥ ይሰራጭ እንደነበር የጣሊያን ሚላን ከተማ የብሔራዊ ካንሰር ኢንስቲትዩት (INT) ጥናት አመልክቷል፡፡ ጥናቱ ከሆነ ኮቪድ-19 ከታሰበው ቀደም ብሎ ከቻይና አልፎ ሳይስፋፋ እንዳልቀረ ያሳያል፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት በታህሳስ ወር በመካከለኛው ቻይና ውሀን ውስጥ የበሽታው ስርጭት ለመጀመሪያ ጊዜ ከመዘገቡ በፊት አዲሱ ኮሮናቫይረስ እና ሲቪአድ -19 የሚያመጣው የመተንፈሻ አካላት በሽታ ያልታወቀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የጣሊያን የመጀመሪያው የኮቪድ-19 ታማሚ በፈረንጆቹ የካቲት 21 ሚላን አቅራቢያ በሰሜናዊው የሎምባርዲ ክልል በምትገኘው ትንሽ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡ ነገር ግን በጥናት ተቋሙ ሳይንሳዊ መጽሔት ቱሞሪ ጆርናል የታተመው የጣሊያን ተመራማሪዎች ግኝት እንደሚያሳየው በፈረንጆቹ መስከረም 2019 እና መጋቢት 2020 መካከል ባለው የሳንባ ካንሰር ምርመራ ሂደት ውስጥ ከተመዘገቡት 959 ጤናማ ፈቃደኞች መካከል 11,6% የሚሆኑት የካቲት በፊት በደንብ የኮሮቫ ቫይረስ ፀረ እንግዳ አካላትን ያዘጋጁ ናቸው ፡፡ ተጨማሪ ልዩ የሳርስ ኮቪድ-2 ፀረ እንግዳ አካላት ሙከራ በሲዬና ዩኒቨርሲቲ በተመሳሳይ ጣልያን ውስጥ “የቅድመ-ወረርሽኝ ጊዜ ውስጥ ሳርስስ-ኮቪ -2 ፀረ እንግዳ አካላት ባልተጠበቀ ሁኔታ መገኘታቸውን” በሚል በዚሁ ርዕስ ምርምር ተካሂዷል ፡፡ ከጥቅምት ወር የመጀመሪያ አራት ሳምንታት ጋር የተዛመዱ አራት ጉዳዮች ቫይረሱ ገለልተኛ ለሆኑ ፀረ እንግዳ አካላትም ተጠቂ ናቸው ፣ ይህም በመስከረም ወር ተይዘዋል ማለት ነው ሲሉ የጥናቱ ባልደረባ የሆኑት ጆቫኒ አፖሎን ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡ አፖሎን “ይህ ዋናው ግኝት ነው-ምንም ምልክት የሌለባቸው ሰዎች ከሴሮሎጂ ምርመራ በኋላ አዎንታዊ ብቻ ሳይሆኑ ቫይረሱን ለመግደል የሚያስችሉ ፀረ እንግዳ አካላትም ነበሯቸው” ብለዋል ፡፡ አዲሱ ኮሮናቫይረስ በሕዝቡ መካከል ለረጅም ጊዜ እና በዝቅተኛ ገዳይነት ሊሰራጭ ይችላል ማለት እየጠፋ ስለሆነ ሳይሆን እንደገና ለማደግ ብቻ ነው ማለት ነው ፡፡ የጣሊያን ተመራማሪዎች በመጪው መጋቢት ወር ውስጥ በሎምበርዲ ውስጥ በከባድ የሳንባ ምች እና የጉንፋን በሽታ ከተያዙት ቁጥር እጅግ ከፍ ያለ መሆኑን የገለጹት ባለፈው መጋቢት ወር ውስጥ አዲሱ ኮሮናቫይረስ ቀደም ሲል ከታሰበው ቀደም ብሎ ሊሰራጭ እንደሚችል የሚያሳይ ምልክት ነው ፡፡
ፖለቲካ
https://am.al-ain.com/article/new-coronavirus-covid19-reported-in-italy-earlier-than-thought-researchers
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
4e7e53ca0ef2eccbcdc8fc3bfcdfcbb7
1f3e27b4276716b76a2c0c879bc81061
የፌዴራል ፖሊስ ወቅቱ የሚጠይቀውን ተቋማዊ ለውጥ እያካሄደ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ባሕር ዳር፡ መስከረም 19/213ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተቋማዊ ለውጥ (ሪፎርም) ሥራዎች ዙሪያ የፓናል ውይይት አካሂዷል፡፡ ‘‘ከራስ በላይ ለሕዝብና ለሀገር” በሚል መሪ ሐሳብ ነው የተካሄደው።በኢትዮጵያ የተደራጀ የፖሊስ ተቋም ታሪክ የ80 ዓመት ዕድሜ ያለው የፌዴራል ፖሊስ በእነዚህ ዓመታት መንግሥታት ሲለዋወጡ የተለያዩ ማሻሻያና አዲስ አደረጃጀቶች እየፈጠረ አሁን ያለበት ቁመና ላይ ደርሷል።በዚህ ወቅትም ዘመኑ የሚጠይቀውን ፈጣን አገልግሎት ለመስጠትና ሀገራዊ ተልዕኮን ለመወጣት የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በተቋሙ ላይ ‘‘ማሻሻያ ያስፈልገኛል’’ ብሎ ወደ ተግባር መግባቱ ተመላክቷል።ወደ ተቋማዊ ለውጥ የገባባቸውን ምክንቶችም ተቋሙ የተቋቋመበትን አዋጅ ጨምሮ መተዳደሪያ ደንቦች መመሪያዎች አሠራርና መዋቅሮችን ተቋሙ አሁን ከሚጠበቅበት ተልእኮ አኳያ ለማስተካከል፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ የወንጀለኞች አቅም በማደጉና ድንበር ዘለል ወንጀሎች በመበራከታቸው እነርሱን መቋቋቀም እንዲቻል፤ ከየትኛውም ወገንተኝነት የጸዳና ሙያ መር የሆነ ፖሊስ ለመገንባት፤ እየተፈጸሙ ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ጊዜ የሚሰጣቸው ባለመሆናቸው፤ የፖሊስን ኑሮ ማሻሻልና ምቹ የሥራ መንፈስ ለመፍጠር የሚሉት እንደሆኑ ተመላክቷል።ዘጋቢ፡- እንዳልካቸው እባቡ -ከአዲስ አበባ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%a8%e1%8d%8c%e1%8b%b4%e1%88%ab%e1%88%8d-%e1%8d%96%e1%88%8a%e1%88%b5-%e1%8b%88%e1%89%85%e1%89%b1-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8c%a0%e1%8b%ad%e1%89%80%e1%8b%8d%e1%8a%95-%e1%89%b0%e1%89%8b%e1%88%9b/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
cd370b940382da78c70a53ee8bce1b01
14ee01dc6c92441deff4a2806f92e415
የሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ለማሻሻል የባለድርሻ አካላት ምክክር ተካሄደ
አዲስ አበባ ፣መስከረም 6 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ለማሻሻል የባለድርሻ አካላት ምክክር በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።በምክክር መድረኩ የሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት የሁለተኛ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን አፈጻጸም ስኬትና ተግዳሮቶች ላይ ውይይት በማድረግ ለቀጣይ አስር ዓመት ዕቅድ ግብዓት የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።በምክክር መድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ማንደፍሮ ንጉሴ ÷ ከሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት አንጻር ባለፉት አምስት ዓመታት የተሰሩ ስራዎችና ያልተሰሩ ስራዎችን በመለየት አፈጻጸሙ ምን እንደሚመስል በመገምገም እና ቀጣይ 10 ዓመት ዕቅድ የተሻለ እንዲሆን የእያንዳንዱ ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።በመሆኑም በውይይቱ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች የሚቀርቡበት ከመሆኑም ባለፈ በ2013 ወደ ተግባር በመቀየር ወደ ስራ መግባት የሚያስችል መርሃ ግብር የሚወጣበት መሆን አለበት ብለዋል።በምክክር መድረኩ ከእርሻ ኢንቨስትመንት ድጋፍ ዳይሬክቶሬት እና ከሀገር አቀፍ የባለሀብቶች ማህበር በኩል በሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት የልማት እንቅስቃሴ የተገኙ ስኬቶችና ልማቱ በዕቅዱ መሠረት ተሰርቶ ለሀገር ኢኮኖሚ ተገቢ አስተዋጽኦ እንዳያበረክት ማነቆች የሆኑ ጉዳዮች ተለይቶ በመንግስት በኩል ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራበት የሚያመላክት ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ችግሮቹም የግብዓት አቅርቦት፣ በቂ መሠረተ ልማት ዝርጋታ አለመኖር፣ የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነትና ፍትሃዊነት ችግር፣ የሚሰራና የማይሰራ ባለሀብት ለይቶ ድጋፍ አለመስጠት እና በአንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ችግሮች መከሰት መሆናቸው ተነስቷል፡፡የፌደራልና የክልል መንግስታት በቅንጅትና በተናበበ መልኩ በመስራትና ክትትልና ድጋፍ በማጠናከር እነዚህንና ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን በመፍታት ሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት በዕቅዱ መሠረት እንዲሰራ ለማድረግ ርብርብ ሊያደርጉ ይገባል ተብሏል፡፡በምክክር መድረኩ የተገኙት የጀርመን አለምአቀፍ ልማት ተራድኦ ድርጅት ተወካይ ድርጅቱ የኢትዮጵያን የሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት ልማት እንዲጠናከር የመንግስትንም ሆነ የግል ባለሀብቶች አቅም ለማሳደግ በተቋማት አቅም ግንባታ፣ በቴክኖሎጂና በፋይናንስ አቅርቦት ለመደገፍና ለማብቃት እና በፖሊሲ ዝግጅት ለማገዝ መዘጋጀቱን መናገራቸውን ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%88%b0%e1%8d%8b%e1%8d%8a-%e1%8a%a5%e1%88%ad%e1%88%bb-%e1%8a%a2%e1%8a%95%e1%89%a8%e1%88%b5%e1%89%b5%e1%88%98%e1%8a%95%e1%89%b5-%e1%8a%a5%e1%8a%95%e1%89%85%e1%88%b5%e1%89%83%e1%88%b4/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b9a7bf901fb921b9409044886e2318fb
7d6fa7eeb28235e298ed5f1b7442e054
ቻይና 206 ሚሊየን ብር የሚያወጣ እህል ለገሰች
የቻይና መንግስት 206 ሚሊየን ብር የሚያወጣ 7ሺህ 408 ሜትሪክ ቶን ስንዴና 579 ሜትሪክ ቶን ነጭ ሩዝ የሰብዓዊ እርዳታ ማድረጉ ተገለጸ፡፡ድጋፉ የተከናወነው ቀደም ሲል የሁለቱ አገሮች መንግስታት ባደረጉት ስምምነት መሰረት ነው፡፡የብሄራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሣ ድጋፉ በሀገሪቱ በተከሰቱ ግጭቶች ለተፈናቀሉ እና ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ለሚኖሩ ዜጎች እንዲውል እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ የቻይና መንግሰትም ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ታን ጂያን በበኩላቸው እንደኢትዮጵያ በማደግ ላይ ያሉ አገራት የምግብ ዋስትናቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ግብርናቸውን ማዘመን እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡በመድረኩ የተሳተፉት ሌሎች አገራትም ከዚህ ቀደም መቶ ሚሊየን የቻይና ገንዘብ ዮዋን በየዓመቱ በቀጣይነት ለመስጠት ቃል ገብተው የነበረ ሲሆን፣ ይህን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈርሟል፡፡ 
ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/32615/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
28cae07d7e18312e53e46c5fac3d3c85
80f871ae75cf55293f5f558a7d71d09a
ፕሬዚዳንት ትራምፕ በፕሬዚዳንትነት የመጀመሪያቸውን የውጭ ሀገር ጉብኝት ሊያደርጉ ነው
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፕሬዚዳንትነት የመጀመሪያቸው የሚሆነውን የውጭ ሀገር ጉብኝት ለማደረግ በዛሬው ዕለት ለመነሳት እየተዘጋጁ ነው፡፡ በፖለቲካ ትርምስ የታመሰውን የዋይት ኃውስን ቤተመንግሥት ትተው ነው የሚጓዙት፡፡አንዳንድ ፖለቲከኞች በአሁኑ ወቅት በዋይት ኃውስ ያለውን ቀውስ ሪቻርድ ኒክሰን ፕሬዚዳንትነትን ካሰወገደው ከዋተር ጌት ቅሌት ጋር እያወዳደሩት መሆናቸውን ዘገቢያችን ጄፍ ካስተር ባጠናቀረው ዘገባ ጠቅሷል፡፡ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/president-donald-trump-visit-5-19-2017/3862588.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
1b0751fbebb0bf7e7c5dcdae89742075
22040ec8e28f1ec14c2b8811e035e28d
የካይዘን ኢንስቲቲዩት በግል እና በተቋም ደረጃ በፍልስፍናው ለተቃኙ አማካሪዎች እውቅና መስጠት ጀመረ
የኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲቲዩት በግል እና በተቋም ደረጃ በፍልስፍናው ተቃኝተው አማካሪ ለመሆን ለሚፈልጉ ምሁራን እውቅና መስጠት መጀመሩን አስታቋል፡፡የኢንስቲቲዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኮከብ ደመቀ  በ2010 የበጀት አመትም በፍልስፍናው ተቃኝተዋል ላላቸው 20 አማካሪዎች ፈቃድ እንደተሰጠም ገልጸዋል፡፡ተቋሙ ፍልስፍናው ያለውን ፋይዳ ለማስፋት በክልሎችና በዩኒቨርሲቲዎች የማስፋፋት ስራዎችን እየሰራ ነውም ብለዋል፡፡እንደ ዶክተር ኮከብ ገለጻ 650 ተቋማት የካይዘን ፍልስፍን ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡በመሆኑም በተያዘው የበጀት ዓመት ከ2.6 ቢሊዮን ብር ማትረፍ መቻሉንም አስረድተዋል፡፡
ቢዝነስ
https://waltainfo.com/am/23447/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
56e21b4347b6c4e26a7b7affc62d8af2
174835e7bdfd1ef1f4bce50b7f5810bb
የሰሜን ጎንደር ዞን ጸጥታ ጉዳዮች መምሪያ ለአካባቢው ሰላም መጠበቅ የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገለጸ
 ህብረተሰቡ በተሳሳተ መረጃ ሳይደናገር የአካባቢውን ሰላም ለመጠበቅ ከጸጥታ ሃይሎ ጎን በመሰለፍ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚባ የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደርና ጸጥታ ጉዳዮች መምሪያ አስታወቀ።የመምሪያው ሃላፊ አቶ መኳንንት መልካሙ በዞኑ ወቅታዊ ሰላምና ማረጋጋት  ዙሪያ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች በአሁኑ ሰዓት የተረጋጋ ሰላም መኖሩን ገልፀዋል፡፡ህብረተሰቡ በአሉቧልታ ወሬ ሳይደናገር መንግስት የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በሚያደርገው ጥረት የጀመረውን ድጋፍና ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡በዞኑ የተፈጠረውን ሰላምና መረጋጋት ለማደፍረስ ''መንግስት ትጥቅ እያስፈታ ነው'' በሚል የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ መሆኑን በመገንዘብ አጥብቆ ሊቃወመው እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡“መንግስት ትጥቅ የማስፈታት አለማ የለውም’’ ያሉት ኃላፊው ከ2007 ጀምሮና ከዛም በፊት ህጋዊ የጦር መሳሪያ ፈቃድ መሰጠቱን አስታውሰዋል፡፡''በጦር መሳሪያው እጅ ከፍንጅ ወንጀል ሲፈጽም እስካልተገኘ ድረስ ህጋዊ የጦር መሳሪያ ፈቃድ ያለው ግለሰብ ትጥቅ እንዲፈታ የተደረገበት ሁኔታ የለም'' ብለዋል ሃላፊው፡፡“በፍርድ ቤት ትእዛዝ ካልሆነና ፖሊስ በጦር መሳሪያ ለተፈጸመ ወንጀል መሳሪያውን በኤግዚቪትነት ለማቅረብ አስገዳጅ ሁኔታ እስካልተፈጠረ ድረስ በማናቸውም ሁኔታ የሰላማዊ ሰዎችን የጦር መሳሪያ ትጥቅ ለማስፈታት አልተሞከረም’’  ብለዋል፡፡በአንዳንዳድ አካባቢዎች የሚስተዋለውን ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ለመግታት መንግስት ተገቢውን ቁጥጥርና ክትትል እያደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ሰሞኑን ''ጅምላ እስር እየተካሄደ ነው'' በሚል የሚናፈሰው ወሬም ከእውነት የራቀ መሆኑን ገልፀው ''የታሰሩት ጥቂት  ግለሰቦችም ቢሆኑ በግርግሩ ወቅት የሰው ሕይወት እንዲጠፋና ንብረት እንዲወድም አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው የታሰሩ ናቸው'' ብለዋል፡፡ማንኛውም ግለሰብ በወንጀል ድርጊት እስካልተሳተፈ ድረስ ስጋት ሊገባው እንደማይገባና አሁን በእስር ላይ የሚገኙትም ቢሆኑ በወንጀል ድርጊቱ እስካልተሳተፉ ድረስ ምርመራው ተጣርቶ ነጻ መሆናቸው ሲረጋገጥ ሊለቀቁ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡ህዝቡ ከምንም በላይ የሰላምን ጠቀሜታ በውል በመገንዘብና ለአፍራሽ ሃይሎች ፕሮፓጋንዳ ጆሮ ሳይሰጥ በአካባቢው የሰፈነው ሰላም እንዲጠናከርና ልማቱም እንዳይደናቀፍ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ኃላፊው አሳስበዋል/ኢዜአ/፡፡
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/28673/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
5a08e9b922e5b7c87652029950717e12
39586cca04c5f76b1c0f4522cb6a67f7
የስሑል ሽረ ተጫዋቾች ቅሬታን እያሰሙ ይገኛሉ
የስሑል ሽረ ተጫዋቾች ለወራት የቆየው የደሞዝ ጥያቄያችን አልተመለሰም በማለት ቅሬታቸው እያሰሙ ይገኛል።በርካታ ክለቦች ከወርሀዊ የደመወዝ ክፍያ ጋር በተገናኘ ጥያቄ እየተነሳባቸው ይገኛል፡፡ ከነዚህም ክለቦች መካከል በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እየተወዳደረ የሚገኘው ስሑል ሽረ ተጫዋቾቹ ከደመወዝ ክፍያ ጋር በተገናኘ ተደጋጋሚ የይከፈለን ቅሬታን እያሰሙ ይገኛሉ። ቁጥራቸው በርከት ያሉ የክለቡ ተጫዋቾች “እስከ አሁን ምንም አይነት ደመወዝ እያገኘን አይደለም። ለክለቡን አመራሮች በተደጋጋሚ እንዲፈፀምልን ብንጠይቅም አጥጋቢ ምላሽን ማግኘት አልቻልንም። አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ ጥያቅያችን ሰሚ አጥቷል።” ሲሉ ለድረ ገፃችን ቅሬታቸውን ገልፀዋል። የተጫዋቾቹ የደመወዝ ክፍያ ከአራት እስከ ስድስት ወራት ያህል ሳይከፈል መቆየቱንም አያይዘው ነግረውናል፡፡ በደሞዙ አለመከፈል ምክንያትም ችግር ውስጥ እንደሆኑ ገልፀው ክለቡ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።በጉዳዩ ዙሪያ የተጫዋቾቹን ጥያቄ ይዘን ምላሽ እንዲሰጡን የክለቡን ስራ አስኪያጅ አቶ ተስፋይ ዓለምን ብንጠይቅም ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ መሆን ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡በአሰልጣኝ ሲሳይ አብርሃም የሚመራው ስሑል ሽረ ምንም እንኳን የ2013 የውድድር ዘመን እጣ ፈንታ ባይታወቅም እስካሁን ምንም አይነት ቅድመ ዝግጅት ካልጀመሩ ክለቦች አንዱ ነው፡፡🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/60104
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
db7cf689592742b4e4c75057e59fe54d
56a98723fb9589c2e9a64c9fd7b92455
ወላይታ
ወላይታ በቀድሞ ሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ባሁኑ ደቡብ ክልል የሚገኝ ና የራሱ የሆነ ቋንቋና ባህል ያለው ሕዝብ ሲሆን ከሲዳማ፡ ከከምባታ፡ ከሃዲያና ተመሳሳይ ቋንቋ ከሚናገሩ ከኩሎ ኮንታ ከጎፋና ጋሞ ሕዝብ ጋር ይዋሰናል። ወላይታ ህዝቡ በጣም የተደባለቀ ሲሆን በከተማ ሆነ በገጠር አከባቢ ልቆ የሚገኝ ኃይማኖት ፕሮቴስታንት ሲሆን ኦርቶዶክስና እስልምና እምነትቶች ይገኙበታል። የወላይታ ዞን አስራ ስድስት ወረዳዎችና ስድስት ከተማ መስተዳደሮች አሉት። እነሱም፦ 1ኛ - ዳሞት ጋሌ ዋና ከተማው ቦዲቲ፡ 2ኛ -ዳሞት ወይዴ ዋና ከተማው፦ በደሳ፡ 3ኛ -ቦሎሶ ሶሬ ዋና ከተማው አረካ፡ 4ኛ -ሁምቦ ዋና ከተማው ጠበላ፡ 5ኛ - ኦፋ ዋና ከተማው ገሱባ፡ 6ኛ- ሶዶ ዙሪያ ዋና ከተማው ሶዶ፡ 7ኛ- ኪንዶ ኮይሻ ዋና ከተማው በሌ፡ 8ኛ- ቦሎሶ ቦምበ ዋና ከተማው ቦምበ እድገት፡ 9ኛ-ዳሞት ሶሬ ዋና ከተማው ጉኑኖ፡ 10ኛ- ዱጉና ፋንጎ ዋና ከተማው ቢጣና፡ 11ኛ ዳሞት ፉላሳ ዋና ከተማው ሻንቶ፡ እና 12ኛ ኪንዶ ዲዳዬ ዋና ከተማው ሀላለ፡ ባይራ ኮይሻ ዋና ከተማው በቅሎ ሰኞ፡ ካዎ ኮይሻ ዋና ከተማው ላሾ፡ አባላ አባያ ዋና ከተማው ፋራቾ፡ ሆቢቻ ባዳ ዋና ከተማው ሆቢቻ ናቸው። ከነዚህም የከተማ መስተዳደሪነት ያገኙ ከተሞች፡ ሶዶ፤ አረካ፤ ቦዲቲ፤ ገሱባ፤ ጉኑኖ እና ጠበላ ናቸው። ወላይታ ከደቡብ ካሉት አከባቢዎች በትምህርት፡ በልማትና በማህበራዊ ሁኔታዎች ልቆ ሊገኝበት የቻለበት ሁኔታዎች ይታያል። ይህም የሆነበት ምክንያት በቀደማዊ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት ምዕራባዊያን በብዛት ገብተው የአከባቢውን ሕዝብ ከመጽሓፍ ቅዱስ ጋር የቀለም ትምህርት አጣምረው ስለሰጡ እድሉን በመጠኑም ቢሆን በመጠቀማቸውና በየጊዜው በአከባቢው የሚመደቡ አስተዳዳሪዎች ጠንካራ በመሆናቸው ነው ይባላል። በቀድሞ ዘመን በወላይታ በርካታ ምሁራን ብቅ ብቅ ብለው ነበር። ከነዚህም ምሁራን በደቡብ ኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው ዶክተርና የጦር ጄኔራል ለመሆኑ የበቁ ብ/ጄኔራል ዶ/ር ጋጋ ኤልጆ በአብይነት ሲጠቀሱ ፦ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ካንገት በላይ ስፔሻሊስት ዶ/ር ታዲዮስ ሙንኤ; ኢትዮጵያ ካሏት ጥቂት የፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች አንዱ የሆኑት ዶ/ር ቀለሙ ደስታ ፡አሜሪካን አገር በዩኒቨርስቲ ኦፍ ፍሎሪዳ ታዋቂ ሓኪምና ረዳት ፕሮፌስር የሆኑ ዶ/ር ይስሓቅ ዳልኬ ናቸው። ዶ/ር ይስሓቅ በትምህርት ውጤታቸው ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ልቀው በመገኘታቸው ከአጼ ኃይለስላሴ እጅ የወርቅ ሰዓት የተሸለሙ 2ኛው የወላይታ ተወላጅ ሲሆኑ ዳዊት ጦሼ ደግሞ የመጀመሪያው ናቸው። የወላይታ ታሪክ ሲወሳ የወላይታ የልማት ሰው በሚል የሚታወቁ ወ/ሰማዕት ስም ሁሌም አብሮ ይወሳል። ደ/ች ወ/ሰማዕት በአስተዳዳሪነት በቆዩበት በአጼ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት ብዙ የልማት ስራዎችን አከናውነዋል። ከሰሯቸው አበይት ስራዎቻቸውም ፦ በጊዜው የነበሩትን ሰባቱንም ወረዳዎች የሚያገናኝ መንገድ አሰርተዋል። በሚሲዮናዊያን አማካኝነት የመጀመሪያውን የደቡብ ሆስፒታል አስገንብተዋል። ወላይታን ከምዕራብ ኢትዮጵያ የሚያገናኝና 90 ሜትር ርዝመት ያለውን ታሪካዊውን የኦሞ ድልድይ አሰርተዋል። ወጣቱ ትርፍ ጊዜውን የሚያሳልፈበትን ወወክማ የወጣቶች መንደር ከዘመናዊ በተ-መጻሕፍት ጋር አሰርተዋል። በሶዶ ከተማ ዘመናዊ የገበያ አዳራሽ ከማሰራታቸው ነው። ከይርጋለም ቀጥሎ በደቡብ የመጀመሪያውን ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አሰርተዋል። ደ/ች ወ/ሰማዕት በወቅቱ ማንም ወጣት የሆነ መንገድ ዳር ቆሞ ሲያወራ ካዩ ይበሳጩ እንደነበርና ከመኪናቸው ወርደው ስራ እንዲሰሩ ወይም ት/ቤት እንዲሄዱ ይመክሩም እንደነበር ይነገርላቸዋል። ደ/ች ወ/ሰማዕት በሰብዓዊ መብት ረገድ ግን ጨቋኝ: ህዝብን የማያከብር: ግብረ-ገብነት የጎደለው ሰው ነው:: ገዥ መደብ ነኝ እያለ የወላይታ አባቶቻችን ሲያሰቃይ ነበሩ:: በ ወ/ሰማዕት ተመቶ የሞቱ ወላይታ አባቶችም እንዳሉ የ ቦጋለ ዋለሉ ቤተሠብ ይናገራሉ:: ባሁኑ ጊዜ ባገር ውስጥና ከአገር ውጭ በተሳተፉበት የሙያ ዘርፍ ሁሉ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር አንቱታን የተጎናጸፉ የወላይታ ተወላጆች ብዛት በርካታ ነው። የውጭ መያያዣ በዉብ ተፈጥሮው እጅግ ብዙ ጎብኚዎች እየሳበ ያለውን የወላይታ አጆራ ፏፏቴ ለማየት ይህን ይጫኑ ወላይታ የኢትዮጵያ ብሔር ነው። ዶ/ር ተመስገን ላንቴራ የኢትዮጵያ ብሔሮች
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
7b539d549a59084edad82e498bbc0d5f
33ce5da14993935f058d42fc9c72653a
ክርስቲያን ጎርኩፍ እና አልጄሪያ ተለያይተዋል 
ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ክርስቲያን ጎርኩፍ ራሳቸውን ከአልጄሪያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝነታቸው ዛሬ በገዛ ፍቃዳቸው አንስተዋል፡፡የ60 ዓመቱ አሰልጣኝ ከአልጄሪያ ሚዲያዎች እንዲለቁ ከፍተኛጫና የደረሰባቸው ሲሆን ዛሬ ከአልጄሪያ እግርኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝደንት መሃመድ ራውራው ጋር ባደረጉት ውይይት የአልጄሪያ ብሄራዊ ብድንን ለቀዋል፡፡ ውይይቱም ጥቂት ደቂቃዎችን ብቻ የፈጀ ነበር፡፡ባሳለፍነው ማክሰኞ አዲስ አበባ ላይ አልጄሪያ ከኢትዮጵያ 3-3 ስትለያይ ብሄራዊ ቡድኑን የመሩት ጎርከፍ ከጨዋታው መጠናቀቅ በኃላ በአሰልጣኝነታቸው መቀጠል እንደሚፈልጉ የገለፁ ቢሆንም ከቀናት ልዩነት በኃላ ስራቸውን ሊለቁ ችለዋል፡፡የሚመርጡት የ4-4-2 አሰላለፍ እና በአልጄሪያ ሊግ ሞቢሊስ የሚጫወቱ ተጫዋቾችን ለብሄራዊ ቡድን አለመምረጣቸው በከፍተኛ ሁኔታ ሲያስወቅሳቸው ነበር፡፡ አብዛኛውን ግዜያቸውን በፈረንሳይ ያሳልፉ የነበሩት ጎርኩፍ የአልጄሪያ የውስጥ ሊግ የመከታተል ዕድል እንዳልነበራቸው ዘገባዎች ጠቁመዋል፡፡የአልጄሪያ የውስጥ ሊግ ላይ የሚጫወቱ ተጫዋቾች በአፍሪካ መድረክ ከ2014 ጀምሮ ስኬታማ ጉዞ ላይ ቢገኙም ጎርኩፍ አሁንም አውሮፓ የሚጫወቱ ተጫዋቾች ላይ ትኩረት አድርገዋል፡፡ ከፌድሬሽኑ ፕሬዝደንት ራውራው ጋርም የነበራቸው ቅራኔ ጎርኩፍ ወደ መውጫው በር እንዲመለከቱ ሳያደርጋቸው እንዳልቀረ ተገልጿል፡፡በ2014 የብራዚል ዓለም ዋንጫ መጠናቀቅ በኃላ ቦሲኒዊውን ቫሊድ ሃሊልሆዚችን ተክተው ወደ ሰሜን አፍሪዊቷ ሃገር የመጡት ጎርከፍ አልጄሪያ በ2015 የአፍሪካ ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ሲያደርሱ ለ2017 የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 10 አናት ላይ አልጄሪያ እንድትቀመጥ አድርገዋል፡፡ እንደ አልጄሪያ እግርኳስ ፌድሬሽን ገለፃ ከሆነ ፌድሬሽኑ ጎርኩፍ ላፈረሱት ውል ምንም ዓይነት ማካካሻ ክፍያ አይቀበልም፡፡ፌድሬሽኑ ቀጣዩን የአልጄሪያ አሰልጣኝ ቪክቶሪያ ላይ ከሲሸልስ ጋር ከሚደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ በፊት ያሳውቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ካልተቻለም ነግሂዝ እና መንሱሪ በግዜዊነት የአሰልጣኝ መንበሩን ይቆናጠቱታል፡፡በምድብ 10 ከኢትዮጵያ ጋር የተደለደሉት ሶስቱም ሃገራት አልጄሪያ፣ ሲሸልስ እና ሌሴቶ ማጣሪያው ከመጠናቀቁ በፊት አሰልጣኞቻቸውን ለውጠዋል፡፡ ሌሴቶ በህዳር ወር ሰፊፊ ማቴቴን በሞሰስ ሲያን እንዲሁም ሲሸልስ ብሩኖ ሳኢንዲኒን በራልፍ ጅያን ሊዊ ተክተዋል፡፡
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/8385
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
74c63454fb6e2e2dc93a8005c18594ed
b022adf4e9a291f8e203e757b17bed7d
ውቅያኖስ
ውቅያኖስ በምድራችን ላይ ትልቁ ውሃማ አካል ነው። በዚህም የመሬት 70.9 በመቶው ክፍል በውሀ የተሸፈነ ነው። በአጠቃላይ 5 ውቅያኖሶች ሲኖሩ እነዚህም፦ ሰላማዊ ውቅያኖስ አትላንቲክ ውቅያኖስ ሕንድ ውቅያኖስ ደቡባዊ ውቅያኖስ አርክቲክ ውቅያኖስ ናቸው። የውሃ አካል
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
e985a51d34c711569c13409481c447f0
21001c9b0e491407b6306f8f99945fb6
በላይቤሪያ የዩኒቨርሲቲ ትምህርት በነጻ ተደረገ
የላይቤሪያው ፕሬዚዳንት ጆርጅ ዊሃ በሁሉም የአገሪቱ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በክፍያ ሲሰጥ የቆየው ትምህርት በነጻ እንዲሆን መወሰናቸውን ከትናንት በስቲያ ይፋ አድርገዋል፡፡በአገሪቱ ትልቁ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሆነውን ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ላይቤሪያን ጨምሮ በአራቱም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ሽራፊ ሳንቲም ሳይከፍሉ በነጻ ትምህርታቸውን መከታተል እንደሚችሉ ፕሬዚዳንቱ ባስተላለፉት መልእክት አስታውቀዋል፡፡ፕሬዚዳንቱ የክፍያ መቅረት ብስራቱን ያሰሙት በመዲናዋ ሞንሮቪያ በሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ላይቤሪያ በመቶዎች ከሚቆጠሩ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ጋር በተገናኙበት አጋጣሚ መሆኑን የዘገበው ቢቢሲ፣ በወቅቱ ተማሪዎቹ በደስታ ምላሽ መስጠታቸውንና በመላ አገሪቱ የሚገኙ በርካታ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም የፕሬዚዳንቱን ብስራት በደስታ እንደተቀበሉት ጠቁሟል፡፡ ፕሬዚዳንት ዊሃም፤ ትምህርት በነጻ እንዲሰጥ ያሳለፉትን ውሳኔ ሌሎች የአፍሪካ አገራትም በአርአያነት ሊከተሉት እንደሚገባ መናገራቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡በአገሪቱ የዩኒቨርሲቲዎች ክፍያ ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉ ተማሪዎችንና ወላጆችን ክፉኛ ሲያስቆጣና አመጽ ሲቀሰቅስ እንደነበር ያስታወሰው የቢቢሲ ዘገባ፣ በቅርቡም የአንድ ክሬዲት አወር ክፍያ በግማሽ ያህል መጨመሩ ተቃውሞ ቀስቅሶ እንደነበር አስታውሷል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=22585:%E1%89%A0%E1%88%8B%E1%8B%AD%E1%89%A4%E1%88%AA%E1%8B%AB-%E1%8B%A8%E1%8B%A9%E1%8A%92%E1%89%A8%E1%88%AD%E1%88%B2%E1%89%B2-%E1%89%B5%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AD%E1%89%B5-%E1%89%A0%E1%8A%90%E1%8C%BB-%E1%89%B0%E1%8B%B0%E1%88%A8%E1%8C%88&Itemid=212
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
98150aeb7b91fa1e1598f859ae40b31a
64a1a65e8f90cef5da049b25caabcd12
በኢትዮጵያ በነሐሴ መጨረሻ ላይ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ወደ ሌላ ጊዜ ከተላለፈ በኋላ በትግራይ በተናጠል የሚካሄደው ምርጫ ሕገ ወጥና ተቀባይነት የሌለው ነው በማለት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቢወስንም ዛሬ እየተካሄደ ነው።
የትግራይ ምርጫ፡ ትልልቆቹ የህወሓት እጩዎች የት ተወዳደሩ?\nለወራት በፌደራሉና በትግራይ ክልል መንግሥት መካከል ያለመግባባት ምንጭ ሆኖ የቆየው ክልላዊው ምርጫ ዛሬ ጳጉሜ 04/2012 ዓ.ም አገሪቱ ካሏት 10 ክልሎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች በተለየ በትግራይ ክልል ውስጥ ይካሄዳል። በዚህ ምርጫ ላለፉት 30 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በብቸኝነት በህወሓት ተይዞ ለቆየው የክልሉ ምክር ቤት መቀመጫዎች 5 ፓርቲዎቹ ይወዳደራሉ። በምርጫው ተቃዋሚዎች ሰምሮላቸው የትኛውንም ያህል መቀመጫ ቢያገኙ በክልሉ ታሪክ በምክር ቤቱ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ከህወሓት ውጪ የሆነ ድምጽ የመሰማት ዕድል ያገኛል። በዚህ ምርጫም ከህወሓት አንጻር በክልሉ የፖለቲካ መድረክ ላይ አዲስ የሆኑት አራት ፓርቲዎች ለፉክክር ቀርበዋል። እነርሱም ሳልሳይ ወያኔ፣ ባይቶና፣ የትግራይ ነጻነት ፓርቲ እና የአሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ሲሆኑ አራት ግለሰቦች በግል ይወዳደራሉ። በምርጫው የሚሳተፉት ፓርቲዎች ባካሄዷቸው ክርክሮች ላይ እንዳንጸባረቁት በተለያዩ መስኮች ካሏቸው ፕሮግራሞች ባሻገር ከማዕከላዊው መንግሥት ጋር ስለሚኖራቸው ግንኙነት አንስተው ዓላማቸውን አንጸባርቀዋል። በዚህም ክልሉ በፌደራላዊ ሥርዓት ከቀሪው የአገሪቱ ክልሎች ጋር ተሳስሮ እንዲቀጥል ከመፈለግ አንስቶ በኮንፌዴሬሽን የላላ ግንኙነት እንዲኖር የሚፈልጉና ከዚህም ከፍ ሲል ነጻ ሪፐብሊክ የመመስረት ፍላጎትም ተንጸባርቋል። በዚህ ምርጫ 190 መቀመጫዎች ላሉት ምክር ቤት 625 እጩዎች ለመወዳደር ቀርበዋል። ከ2.7 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ድምጽ ለመስጠት እንደተመዘገበ ያስታወቀው የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን ድምጽ መስጠቱ የሚከናወንባቸው 2684 የምርጫ ጣቢያዎች እንዳሉ አስታውቋል። ክልሉ ምርጫውን እንዲያስፈጽምለት ብሔራዊውን የምርጫ ቦርድን ቢጠይቅም ካለው የወረርሽኝ ሁኔታ አንጻር በመላው አገሪቱ ከተወሰነው ውጪ ምርጫውን ማካሄድ እንደማይችል አሳውቆ ጥያቄውን ሳይቀበለው መቅረቱ ይታወሳል። በዚህም ምክንያት ነበር ክልሉ ከራሱ በጀት በማውጣት የምርጫ ኮሚሽን መስርቶ ምርጫውን ለማካሄድ በመወሰን ከዛሬው የድምጽ መስጫ ቀን ላይ የተደረሰው። ዋነኞቹ የህወሓት እጩዎች በፌደራል መንግሥቱና በተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራቸው ዋና ዋና የህወሓት አባላት በዚህ በምርጫው በተለያዩ ጣቢያዎች ከተፎካካሪዎቻቸው ጋር ለውድድር ቀርበዋል። የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንትና የህወሓት ሊቀመንበር የሆኑት ደብረጽዮን ገብረሚካኤል፣ በአድዋ ከተማ ፓርቲያቸውን ወክለው ሲወዳደሩ፣ እዚያው አድዋ ውስጥ ባሉ ቦታዎች ላይ ደግሞ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበርና የቀድሞዋ የንግድ ሚኒስትር ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ) እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የነበሩት አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ ይወዳደራሉ። በመቀለ የምርጫ አካባባቢ ህወሓትን ወክለው ከሚወዳደሩት መካከል በገዛ ፈቃዳቸው ኃላፊነታቸውን ከጥቂት ወራት በፊት የለቀቁት የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም፣ በሕግ የሚፈለጉት የቀድሞው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ዋና ዳይሬክተር የአቶ ጌታቸው አሰፋ ወንድም ዳንኤል አሰፋ በዕጩነት ቀርበዋል። የአዲግራት ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክትር ዛይድ ነጋሽ በአዲግራት የህወሓት እጩ ሆነው ቀርበዋል። የቀድሞው የኮሙኑኬሽን ሚኒስትርና በተለያዩ የማዕከላዊው መንግሥት ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የሰሩት አቶ ጌታቸው ረዳ ህወሓትን ወክለው አላማጣ ውስጥ ሲቀርቡ የመቀለ ዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ክንደያ ገብረሕይወት (ፕሮፌሰር) እንደርታ በመቀለ አካባቢ ቀርበዋል። በተለያዩ የምርጫ አካባቢዎች ህወሓት ከተጠቀሱት በተጨማሪ በርካታ እጩዎችን ያቀረበ ሲሆን፣...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
e465b737042175757280ce9b73da9767
3cb0f9775d1502730b5f6249c5bba606
ግዑዝነት
ግዑዝነት ማለት ቁስ ነገሮች የሚገኙበት ፍጥነት እንዳይለወጥ የሚያደርጉት ተቃውሞ ነው። አካላት አርፈው ተቀምጠውም እንደሆነ ባሉበት እንዲሆኑ፣ በቀጥታ እየተጓዙም እንደሆነ፣ አቅጣጫቸውን ሳይቀይሩ ባሉበት ፍጥነት እንዲቀጥሉ ያላቸው ፍላጎት ወይም አዝማሚያ ግዑዝነታቸው ይባላል። ግዑዝነት የቁሶች ወይንም ግዝፈት ያላቸው ነገሮች ሁሉ ዋና መገለጫ ባህሪ ነው።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
e1cef83b522cc9c953fe0a3c0d7634a0
aa2661bfa9fbd3fa8af02f9ed45dcd46
ኮሮናቫይረስ፡ ብዙ ያልተነገረለት ኮቪድ-19 በአንጎላችን ላይ ሊያደርስ የሚችለው ጉዳት ምንድን ነው?
ዶክተር አርቪንድ ቻንድራቴቫ የተጎዳ የአንጎል ክፍልን በምስል ሲያሳዩ እያንዳንዱ ሳምንት ባለፈ ቁጥር ኮሮናቫይረስ ዘርፈ ብዙ አእምሯዊና አካላዊ ጉዳቶችን ማስከተል ይጀምራል። ቫይረሱ እንደተገኘባቸው የተረጋገጡ በርካታ ሰዎች በመጀመሪያ አካባቢ ብዙም የሚሰጋ ህመም የማይሰማቸው ሲሆን፤ ቀስ በቀስ ግን ማስታወስ አለመቻልና ድካምን የመሳሰሉ ጠንከር ያሉ ምልክቶች ማሳየት ይጀምራሉ። ፖል ማይልሪያ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሁለት ከባድ የሚባሉ ስትሮኮች [የአንጎል ውስጥ ደም መፍሰስ] አጋጥመውታል። የ64 ዓመቱ ፖል በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የኮምዩኒኬሽንስ ኃላፊ ሲሆን እምብዛም ስጋት ውስጥ ሊከተው ሚችል የጤና እክል አልነበረበትም። በለንደኑ የአንጎልና የአንጎል ቀዶ ህክምና ብሔራዊ ሆስፒታል ውስጥ እጅግ ከፍተኛ የጤና መሻሻል ያሳየ የኮሮረናቫይረስ ታማሚ ሆኗል። ካጋጠመው ስትሮክ በኋላም ፖል ጥሩ የሚባል መሻሻል ታይቶበታል። የመጀመሪያው ስትሮክ ያጋጠመው በሆስፒታል የጽኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ እያለ ነበር። በዚህ ምክንያት ሕይወቱ ልታልፍበት የምትችለበት እድልም ከፍተኛ ነበር። ለዚህም ሲባል ደም የሚያቀጥን መድኃኒት እንዲወስድ ተደርጎ ነበር። ከጥቂት ቀናት በኋላ ደግሞ ለሁለተኛ ጊዜ ስትሮክ አጋጠመው። ሁለተኛው ግን በጣም የከፋና ሕይወቱን ትልቅ አደጋ ውስጥ የከተተ ነበር። አማካሪ የአንጎል ሐኪም ሆኑት ዶክተር አርቪንድ ቻንድራቴቫ፤ ፖል በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታሉ ሲመጣ ሥራቸውን ጨርሰው እየወጡ ነበር። ''ፖል ፊቱ ላይ ግራ መጋባት ይስተዋልበት ነበር። መመልከት የሚችለው በአንድ አቅጣጫ በኩል ብቻ ነበር፤ ተንቀሳቃሽ ስልኩን ለመጠቀምም ሲቸገርና የይለፍ ቃሉን ማስታወስ አቅቶት ግራ ሲጋባ ነበር'' ብለዋል ዶክተሩ። ዶክተር አርቪንድ እንደሚሉት በፖል ጭንቅላት ውስጥ አጋጥሞ የነበረው የደም መርጋት ከዚህ በፊት አይተውት የማያውቁት አይነት እንደሆነ ይናገራሉ። ፖል በተደረገለት ምርመራ የደም መርጋት ምልክቶች ታይተውበታል። በምርመራው የተገኘው ውጤትም አጋትሟቸው በማያውቁት ሁኔታ እጅግ የተለየና አሳሳቢ ነበር። "በሕይወቴ እንዲህ ያለ ውስብስብና ከፍተኛ ከፍተኛ ደም መርጋት ሁኔታ ተመልክቼ አላውቅም" የሚሉት ዶክተር አርቪንድ ኮሮረናቫይረስ የፖል ደም በእጅጉ የተጣበቀ እንዲሆን እንዳደረግ ይገልጻሉ። በእንቅስቃሴ ገደቡ ጊዜ ስትሮክ አጋጥሟቸው ድንገተኛ ክፍል የሚገቡ ሰዎች ቁጥር ቀንሶ ነበር። ነገር ግን በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ የአንጎል ህክምና ባለሙያዎች በኮቪድ-19 ምክንያት ስትሮክ ያጋጠማቸው ስድስት ሕመምተኞችን አክመዋል። ለአደጋው መንስኤ የነበረው በሰውነት እና በአንጎል ውስጥ እብጠት የሚያስከትሉ የሰውነት በሽታ ተከላካይ ሕዋሳት በጣም ከመጠን በላይ መበራከት ነው። ዶክተር አርቪንድ የፖልን አንጎል የውስጥ ክፍልን የሚያሳዩ ምስሎችን ሲመለከቱ በቫይረሱ ምክንያት የማየት አቅሙ መዳከሙን፣ ማስታወስ እንደሚቸግረው፣ መናገር እንደሚከብደውና ነገሮችን ማስተዋል ከባድ እንደሚሆንበት አስተውለዋል። ያጋጠመው ስትሮክ በጣም ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ሐኪሞች በሕይወት አይተርፍም ወይም የአካል ጉዳተኛ ይሆናል ብለዋ ገምተው ነበር። ፖልም ቢሆን "ከሁለተኛው ስትሮክ በኋላ ባለቤቴ እና ሴት ልጆቼ አበቃለት ብለው እንደገና ደግመው እንደማያዩኝም ገምተው ነበር'' ሲል ተናግሯል። ''ዶክተሮቹ ምንም ማድረግ የሚችሉት ነገር እንደሌለና ያለው አማራጭ መጠበቅ ብቻ እንደሆነ ነገሯቸው። ነገር ግን እኔ በሆነ መንገድ ተረፍኩኝ፤ ጤናዬም ቀስ በቀስ መስተካከል ጀመረ።'' ፖል ማይልሪያ ከስትሮክ ካገገመ በኋላ ፖል እየተሻለው መሆኑን ካሳዩ ነገሮች መካከል ከነርሶቹ ጋር በእንግሊዝኛ የጀመረውን ንግግር...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
d7b7b6c5c7ea8f97731dc4fb4f4c77d9
0cb43163c24e08b1138b6d7e02b83be2
ስኳር ኮርፖሬሽን በአገሪቱ የስኳር እጥረት የለም አለ
ንግድ ሚኒስቴርን ጨምሮ ሁሉም የከተማና የክልል ንግድ ቢሮዎች ስኳር በኮታ እያደሉ ቢሆንም፣ ስኳር ኮርፖሬሽን በየወሩ 569 ሺሕ ኩንታል እያቀረበ መሆኑንና የክምችት ችግር እንደሌለበት አስታወቀ፡፡      ስኳር ኮርፖሬሽን 200 ለሚጠጉ የቢራ፣ የለስላሳ፣ የምግብ፣ የከረሜላና እንዲሁም ለምርቶቻቸው ስኳር ለሚፈልጉ ኢንዱስትሪዎች በየወሩ 170 ሺሕ ኩንታል ያቀርባል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ አሥር ክፍላተ ከተሞች 112 ሺሕ ኩንታል ስኳር፣ ለክልሎች ደግሞ 287 ሺሕ ኩንታል ያቀርባል፡፡      በንግድ ሚኒስቴር አማካይነት በወጣው ኮታ መሠረት የክልል ቢሮዎች በኅብረት ሥራ ማኅበራት፣ በሸማቾች ማኅበራት፣ በቀድሞዎቹ ኢትፍሩትና ጅንአድ አማካይነት ለተጠቀሚዎቹ ያከፋፍላሉ፡፡የስኳር ኮርፖሬሽን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ጋሻው አይችሉም ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ እስካሁን ኮርፖሬሽኑ የስኳር እጥረትን በተመለከተ የቀረበለት ሪፖርት የለም፡፡‹‹የአቅርቦትም የክምችትም ችግር የለብንም፡፡ ፍላጎት ማርካት ካልተቻለ እንኳ ከውጭ እናስገባለን፤›› ሲሉ አቶ ጋሻው ተናግረዋል፡፡በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ በሚገኙ የስኳር ፋብሪካዎች ከ3.5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ያመርታሉ፡፡ ፍላጎቱን ለማሟላት ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ስኳር ወደ አገር ውስጥ ይገባል፡፡ ይህ መጠን በፍላጎትና በአቅርቦት መካከል ክፍተት እንዳይኖር ያደርጋል ተብሏል፡፡በሚቀጥለው 2010 በጀት ዓመት ደግሞ ነባሮቹን ጨምሮ ስምንት ስኳር ፋብሪካዎች ወደ ምርት እንደሚገቡ፣ የአገሪቱ የማምረት አቅምም ሰባት ሚሊዮን ኩንታል እንደሚደርስ ተገልጿል፡፡ነገር ግን ስኳር በበቂ ሁኔታ እየደረሰ አለመሆኑን የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች እየገለጹ ነው፡፡ በተለይ ሰሞኑን በኬንያ መንግሥት ጥያቄ መሠረት ከኢትዮጵያ 44 ሺሕ ኩንታል ስኳር ወደ ጂቡቲ መላኩ በብዙዎች ዘንድ አግራሞትን ፈጥሯል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ፣ ከተለያዩ ክፍላተ ከተሞች በተለይ የስኳርና የዘይት እጥረት እየገጠመ መሆኑ ሪፖርት እየቀረበለት ነው፡፡ይህንን ችግር ለመፍታት ቢሮው የተለያዩ ሥራዎችን ሲያከናውን ቢቆይም፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ‹‹የመሠረታዊ ሸቀጣ ሸቀጥ አባወራና እማወራ ከቸርቻሪ ሱቆች ጋር ለማስተሳሰር የተዘጋጀ የሥርጭት ካርድ›› የሚል የግብይት ካርድ ማደል ጀምሯል፡፡የሥርጭት ካርዱ እንደሚያብራራው አንድ አባወራ/እማወራ ወርኃዊ የስኳር ኮታ አምስት ኪሎ ግራም፣ የዘይት ኮታ ደግሞ እስከ አምስት ሊትር ድረስ ነው፡፡ የዘይት መጠኑ እንደየአቅርቦቱ የሚለያይ ይሆናል ይላል፡፡‹‹የሥርጭቱ ካርድ በየ15 ቀናት ወይም በወር ለአንድ ጊዜ ግብይት የሚያገለግል ነው፤›› ይላል አዲሱ የግብይት ካርድ፡፡ ይህ አዲስ የመገበያያ ካርድ የተዘጋጀው ነዋሪዎች በአካባቢያቸው ካለ መደብር እንዲገበዩ ለማድረግና ክልከላን ለማስቀረት የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይህ አሠራር በቅርቦትና በፍላጎት መካከል አለመጣጣም መኖሩን ያሳያል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ምንጮች ለሪፖርተር እንደሚገልጹት ግን፣ በዚህ ንግድ ዘርፍ የአየር በአየር ንግድ በመኖሩና በኮንትሮባንድ ስኳር ከአገር የሚወጣ በመሆኑ ለነዋሪዎች ተደራሽ ለማድረግ ጠቃሚ እንደሆነ ይሞግታሉ፡፡ኤክስፖርቱን በተመለከተ አቶ ጋሻው ሲያስረዱ፣ በዓለም ብራዚልና ታይላንድ ብቻ ስኳር ወደ አገራቸው አያስገቡም፡፡ ሌሎች አምራች አገሮች ግን ጥሩ ዋጋ ሲያገኙ ኤክስፖርት ያደርጋሉ፡፡ በአገራቸው እጥረት ሲከሰት ደግሞ ጥሩ ዋጋ ከሚያገኙበት ገበያ ኢምፖርት ያደርጋሉ፡፡ ኮርፖሬሽኑ በዚህ መሠረት በአገሪቱ ካለው ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት ስትራቴጂ መንደፉን አቶ ጋሻው ገልጸዋል፡፡‹‹የኬንያ ጥያቄ የመጣው ይህንን ስትራቴጂ በነደፍንበት ወቅት ነው፤›› ሲሉ አቶ ጋሻው የኮርፖሬሽኑን ሐሳብ ገልጸዋል፡፡ ለኢትዮጵያ ምርቶች አዲስ ገበያ እየሆነች ወደመጣችው ኬንያ ስኳር በ110 ተሽከርካሪዎች እየተጓዘ ባለበት ወቅት ግን ችግር አጋጥሞ ነበር፡፡ለችግሩ መነሻ የሆነው ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ በሚወስደው መንገድ ላይ አንድ ከባድ ተሽከርካሪ ከ280 ኩንታል በላይ መጫን አለመቻሉ ነው፡፡ ነገር ግን ከወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የተነሱት ከባድ ተሽከርካሪዎች 400 ኩንታል ጭነው፣ አስፈላጊውን ሰነድ አሟልተው፣ እንዲሁም ተሽከርካሪዎቹ ለቆሙበት ዴሚሬጅ የሚከፍለው አካል ባለመለየቱ ለቀናት ተጉላልተው እንደነበር ታውቋል፡፡አቶ ጋሻው እንዳሉት ይህ ችግር ተፈትቶ ሐሙስ ነሐሴ 25 ቀን 2009 ዓ.ም. ተሽከርካሪዎቹ ወደ ኬንያ ጉዞ ማድረግ ጀምረዋል፡፡  
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%88%B5%E1%8A%B3%E1%88%AD-%E1%8A%AE%E1%88%AD%E1%8D%96%E1%88%AC%E1%88%BD%E1%8A%95-%E1%89%A0%E1%8A%A0%E1%8C%88%E1%88%AA%E1%89%B1-%E1%8B%A8%E1%88%B5%E1%8A%B3%E1%88%AD-%E1%8A%A5%E1%8C%A5%E1%88%A8%E1%89%B5-%E1%8B%A8%E1%88%88%E1%88%9D-%E1%8A%A0%E1%88%88
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
de89880e12b0ad426e571dae402d19d2
f86c6eb12477dd6f093ef46769396235
እውቁ አሜሪካዊ ተዋናይና ፕሮድዩሰር ድዋይን ዳግላስ ጆንሰን፤ በቅፅል ስሙ 'ዘ ሮክ' በህዋይ በተካሄደ ሚስጢራዊ የሠርግ ሥነ-ሥርዓት ለረዥም ዓመታት ፍቅረኛው ከነበረችው ሎረን ሃሺያን ጋር በጋብቻ መተሳሰሩ ተነገረ።
ዕውቁ አሜሪካዊው ተዋናይ ዘ ሮክ በሚስጢር ተሞሸረ\n• ፍቅርና ጋብቻ በቀይ ሽብር ዘመን • ከስም ፊት የሚቀመጡ መለያዎና አንድምታቸው የ47 ዓመቱ ጎልማሳ ዘ ሮክ ይህንን ዜና ይፋ ያደረገው 154 ሚሊየን ተከታዮች ባሉት የኢንስታግራም ገፁ ላይ ነው። ጥንዶቹ ላለፉት 13 ዓመታት የዘለቀ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን ግንኙነቱን የጀመሩት 'ዘ ጌም ፕላን' የተሰኘውን ፊልሙን በመቅረፅ ላይ ሳለ ነበር፤ ከዚያም የሁለት ልጆች ወላጆች ለመሆን በቅተዋል። ታዲያ ይህንን ሚስጥራዊ የሠርግ ሥነ ሥርዓታቸውን የሚያሳየው ፎቶግራፍ በኢንስታግራም ከተለቀቀ በኋላ በሦስት ሰዓታት ውስጥ ከሰባት ሚሊየን በላይ ሰዎች ወደውታል። የዓለማችን ዝነኛ የፊልም ኮከብ ዘ ሮክ [በመዝገብ ስሙ ድዋይን ጆንሰን] ከሆሊውድ እውቅ ተዋናዮች የእንኳን ደስ አለህ መልዕክቶችም ጎርፈውለታል። በፎቶግራፉ ላይ አስተያየታቸውን ከሰጡት የሆሊውድ ኮከቦች መካከል ራያን ሬይኖልድስ፣ ካረን ጊላን፣ ፒ ዲዲ፣ ጀሲካ ቸስቴይን፣ እና ናኦሚ ካምፕቤል ይገኙበታል። • ፍቅር እና ግንኙነት ከቲንደር አብዮት በኋላ ባለቤቱ ሎረን በ1980ዎቹ በነበሩት ሙዚቃዎች በቦስተን ባንድ በተሰራው 'ሞር ዛን ኤ ፊሊንግ' ሙዚቃ አባቷ ድራም ተጨዋች ነበሩ። እሷም ሙዚቀኛ ስትሆን በኦንላይን በምትለቃቸው የሙዚቃ ሥራዎች ትታወቃለች። ይህ ለ ዘ ሮክ ሁለተኛ ጋብቻው ነው ። ከመጀመሪያው ሚስቱ ዳኒይ ጋርሺያ ጋር በአውሮፓዊያኑ 1997 ትዳር መስርተው 18 ዓመት ወጣት ልጅ አድርሰዋል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
97b9250b2cc9e648f4a8d4d9d518961b
f7b8fd1b425ad52400e9771dde253013
ሪፖርት | የፍቅረየሱስ ድንቅ ግብ ለሀዋሳ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አስጨብጣለች
በመጀመሪያዎቹ 15 ደቂቃዎች ላይ ሁለቱም ቡድኖች ጥንቃቄ መርጠው የተንቀሳቀሱ ሲሆን ሀዋሳ ከተማዎች እንደሁልጊዜው ሁሉ በኳስ ቁጥጥር የበላይነቱን ወስደዋል፡፡ በ5ኛው ደቂቃ ላይ ፍሬው ሰለሞን ወደ ሳጥን ውስጥ እየገፋ ገብቶ ወደ ግብ የሞከራት ኳስ አቅጣጫዋን ስታ ወደ ውጭ የወጣችው ኳስ በሀዋሳ በኩል ፤ ጌታነህ ከበደ ከርቀት መትቶ ኢላማው ሳይጠብቅ የወጣበት ሙከራ በመጀመርያዎቹ ደቂቃዎች የሚጠቀሱ የግብ አጋጣሚዎች ነበሩ፡፡ ከ15ኛው ደቂቃ በኃላ የጨዋታውን መንፈስ የቀየሩ ድርጊቶች በስታዲየሙ ሲስተዋሉ ተመልክተናል፡፡ ዳንኤል ደርቤ ወደ ደደቢት የሜዳ ክፍል ኳስን እየነዳ ሲገባ ብርሀኑ ቦጋለ በእጅ ነክቷል በሚል ሀዋሳዎች የቅጣትምት ቢጠብቁም ረዳት ዳኛው ኃይለራጉኤል ወልዳይ ኳሱን የነካው ዳንኤል ነው በሚል ለደደቢት ቅጣት ምት በመስጠት ጨዋታው ሲቀጥል የሀዋሳ ከተማ ደጋፊዎች ተቃውሟቸውን ውሀ ያዘለ ፕላስቲክ በመወርወር አሰምተዋል፡፡ ከዚህች ድርጊት በኃላም ከጨዋታው እንቅስቃሴ ይልቅ የሚፈጠሩት አላስፈላጊ ድርጊቶች አመዝነው ታይተዋል፡፡በ18ኛው ደቂቃ ዳዊት ፍቃዱ ወደ ደደቢት የግብ ክልል እየገፋ ገብቶ በነፃ አቋቋም ለነበረው እስራኤል እሸቱ ሰጥቶት ወጣቱ አጥቂ ሞክሮወደ ውጪ ሲወጣበት በ21ኛው ደቂቃ ላይ ፍሬው ሰለሞን መሀል ለመሀል አሾልኮ የሰጠውን ኳስ ዳዊት ፍቃዱ እየገፋ ገብቶ ከግብ ጠባቂው አማራ ክሌመንት ጋር አንድ ለአንድ ቢገናኝም ክሌመንት አዞንቶ በግሩም ሁኔታ መልሶበታል፡፡ በ40ኛው ደቂቃ ላይ የተገኘችውን ቅጣት ምት ፍሬው ሰለሞን በቀጥታ መቶ ለጥቂት ወደ ውጪ የወጣበትም በመጀመርያው አጋማሽ በባለሜዳዎቹ በኩል የሚጠቀሱ የግብ ሙከራዎች ነበሩ፡፡ ደደቢት በተቃራኒው ደካማ የማጥቃት አቀራረብ የነበረው ሲሆን ገና በጊዜ አቤል ያለውን በጉዳት ማጣታቸው ይበልጥ እንዲዳከሙ እና በጠንካራነቱ የሚጠቀስ የግብ አጋጣሚ እንዳይፈጥሩ አድርጓቸዋል፡፡በዝናብ የታጀበው የሁለተኛው የጨዋታ አጋማሽ በሚፈጠሩ ውዝግቦች መቆራረጥ የበዛበት ነበር፡፡ በተለይ የሀዋሳ ከተማ ደጋፊዎች በ17ኛው ሳምንት ወደ ወልዲያ አምርተው 1 ለ 1 በተለያዩበት ጨዋታ ክለባችን ላይ ለተፈፀሙ ድርጊቶች ፌድሬሽኑ አፋጣኝ ውሳኔ ሊሰጥ ይገባል የሚል ቅሬታን አሰምተዋል፡፡ በዚህ የጨዋታ አጋማሽ ደደቢቶች በተሻለ መልኩ የተንቀሳቀሱበት ቢሆንም ሀዋሳዎች የኳስ ቁጥጥር የበላይነቱን በዚህም አጋማሽ ወስደዋል፡፡51ኛው ደቂቃ ላይ በጨዋታው ጥሩ ሲንቀሳቀስ የነበረው ፍሬው ሰለሞን በግል ጥረቱ የሰጠውን ኳስ እስራኤል እሸቱ ቢያገኛትም ሳይጠቀምበት የቀረው ኳስ የሁለተኛው አጋማሽ የመጀመርያ ሙከራ ሲሆን 53ኛው ደቂቃ ላይ እንግዳው ቡድን ደደቢት በሽመክት ጉግሳ አማካኝት የግብ እድል አግኝቶ ዳንኤል ደርቤ ደርሶ አስጥሎታል፡፡ 59ኛው ደቂቃ ላይ ፍቀረየሱስ ከርቀት የመታትን ኳስ አማራ ክሌመንት ተወርውሮ ሲያወጣበት በ63ኛው ደቂቃ ላይ ኤፍሬም ያሸገረውን ኳስ ለጌታነህ ከበደ ሰጥቶት ከግብ ጠባቂው ሶሆሆ ሜንሳ ጋር አንድ ለአንድ የተገናኘው ጌታነህ አገባው ተብሎ ሲጠበቅ ሶሆሆ በግሩም ብቃት አድኖበታል፡፡በጨዋታው የመጨረሻዎቹ 30 ደቂቃዎች ሀዋሳ ከተማዎች ግብ ለማስቆጠር ጫና ፈጥረው ተጫውተዋል፡፡ በሁለተኛው ዙር ከተስፋ ቡድን ያደገው ቸርነት አውሽ እና አላዛር ፋሲካን ቀይረው ካስገቡ በኃላም በተሻለ መልኩ ለግብ የቀረቡ አጋጣሚዎችን መፍጠር ችለዋል፡፡ 68ኛው ደቂቃ ላይ ቸርነት አውሽ እና ፍሬው ሰለሞን በአንድ ሁለት ቅብብል ወደ ሳጥን በመግባት የተሻገረውን አላዛር ፋሲካ በግልፅ ሁኔታ አግኝቶ ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡ የሀዋሳዎች ተደጋጋሚ ጫና በመጨረሻም ወደ ውጤታማነት ተለውጦ በ80ኛው ደቂቃ ላይ ሙሉዓለም ረጋሳ ያሻገረውን ኳስ ፍቅረየሱስ ተወልደብርሃን የደደቢት ተጫዋቾችን በማለፍ አማራ ክሌመንትን ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ አስቶ ግብ በማስቆጠር ቀዳሚ መሆን ችለዋል፡፡ከጎሉ መቆጠር በኋላ ተጨማሪ ግብ ሊሆኑ የሚችሉ እድሎች ሳይፈጠሩ ሀዋሳ ከተማ መሪኑን በማስጠበቅ 1-0 በሆነ ውጤት አሸንፎ ወጥቷል፡፡ በውጤቱ መሰረት መሪው ደደቢት ከተከታዮቹ ያለውን ልዩነት ያስፋት እድሉን ሳይጠቀምበት ሲቀር ሀዋሳ ከተማ ነጥቡን 25 በማድረስ ራሱን ከመሪዎቹ አስጠግቷል፡፡ጨዋታው ለኛ ከባድ ነበር፡፡ ያለፈው የወልዲያ ጨዋታ ላይ በርካታ ጉዳቶች ነበሩብን፡፡ ድካም ነበር ፤ ከዛ አንፃር ጫና ነበረው፡፡ በኛ በምንፈልገው አንፃር ተጫውተናል ማለት ይከብደኛል፡፡ ከረፍት መልስ በተወሰነ መልኩ ተጫዋቾች ቀይረን አስገብተናል፡፡ ካለመረጋጋት ያመከናቸው በርካታ አጋጣሚዎች ነበሩ ፤ ሰአቱ እየገፋ በሄደ ቁጥር ደግሞ ተጫዋቾቼ ለግብ ማስቆጠር የነበራቸው ጉጉት ከፍተኛ ነበር፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን በማሸነፋችን ደስ ብሎኛል፡፡ጨዋታው ጥሩ ነበር፡፡ ሁለቱም ኳስ የሚጫወት ቡድን ናቸው፡፡ ነገር ግን ደጋፊው የፈጠረው ተፅእኖ እኛን አዘናግቶናል፡፡ ሀዋሳ በመጀመሪያ አጋማሽ ጥሩ ነበሩ፡፡ በሁለተኛው አጋማሽ ደግሞ እኛም ጥሩ ነበርን፡፡በኢንተርኔት መቆራረጥ ምክንያት ሪፖርቱን በወቅቱ ማቅረብ አልቻልንም።
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/35422
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
19836a246f73d3609c172050f6a83c3c
c6b945a95d5694f4f6b6e5f08721c2c1
በኤርትራ በኮሮናቫይረስ የተያዘ የመጀመሪያው ሰው ተገኝቷል
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኤርትራ በኮሮናቫይረስ የተያዘ የመጀመሪያው ሰው ተገኝቷል።ቫይረሱ የተገኘበት ግለሰብ ዛሬ ጠዋት ከኖርዌይ የገባ መሆኑን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።የ39 ዓመት እድሜ ያለው ግለሰቡ ኤርትራዊ እንደሆነና በቋሚነት በኖርዌይ እንደሚኖረ የሀገሮቱ የኢንፎረሜሽን ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ማምሻውን አስታውቀዋል።ዛሬ በአስመራ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በተደረገ የሙቀት ልኬት ተለይቶ በላብራቶሪ ምርመራ ቫይረሱ እንደሚገኝበት ከተረጋገጠ በኋላ ግለሰቡ በለይቶ ማቆያ ውስጥ አስፈላጊው የህክምና ክትትል እየተደረገለት ይገኛልም ነው የተባለው።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%8a%a4%e1%88%ad%e1%89%b5%e1%88%ab-%e1%89%a0%e1%8a%ae%e1%88%ae%e1%8a%93%e1%89%ab%e1%8b%ad%e1%88%a8%e1%88%b5-%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8b%ab%e1%8b%98-%e1%8b%a8%e1%88%98%e1%8c%80%e1%88%98/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
43067379af69bebf820344811e9b93cb
deff3907409639efba9fb0b2ea57945c
የጣሊያን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው
የጣሊያኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ጄንቲሎኒ ዛሬ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ፓውሎ ጄንቲሎኒ በኢትዮጵያ ለአንድ ቀን በሚያደርጉት ጉብኝት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖምና ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር የሁለቱን አገራት ትብብር ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡እንደ ኢዜአ ዘገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ፓውሎ ጄንቲሎኒ ዛሬ ከእኩለ ቀን በኋላ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/25243/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
ec64ee298eaf1cc44003b41345ca58f3
44141ded8df49e1cefa780476f153380
የግል ትምህርት ቤቶች 3ሺህ 753 ተማሪዎችን በነፃ ለማስተማር ወሰኑ
አዲስ አበባ፡- በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ገቢያቸው ለቀነሰባቸው ወላጆችን ለመደገፍ 39 የግል ትምህርት ቤቶች 3ሺ 753 ተማሪዎችን በነፃ ለማስተማር መወሰናቸውን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ሥልጠና ጥራት የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ባለሥልጣን አስታወቀ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ሥልጠና ጥራት የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ባለሥልጣን ኃላፊ ወይዘሮ ሸዊት ሻንካ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ የኮሮና ቫይረስ ያመጣውን ተጽእኖ ተከትሎ በርካታ የግል ትምህርት ቤቶች ከ50 እስከ 75 በመቶ ክፍያ እንዲቀበሉ እየተደረገ ይገኛል። ከዚህ ባለፈ ግን የችግሩን ግዝፈት በመመልከት በበሽታው ምክንያት ገቢያቸው የቀነሰባቸውን ወላጆች ጫና ለመቀነስ 3ሺ 753 ተማሪዎችን በነፃ ለማስተማር ውሳኔ ያስተላለፉ የግል የትምህርት ተቋማት 39 ደርሰዋል። እንደ ወይዘሮ ሸዊት ገለጻ፤ የግል ትምህርት ቤቶቹ ከወላጅ ኮሚቴዎች ጋር በመነጋገር እና ገቢያቸው የቀነሰባቸውን ወላጆች ልየታ በማድረግ ተማሪዎቻቸውን በነፃ ለማስተማር ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ለአብነት በኮልፌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ የግል ትምህርት ተቋማት ከወላጅ ኮሚቴዎች ጋር ባደረጉት ውይይት 696 ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድሉ እንዲሰጣቸው ስምምነት አድርገዋል። በአቃቂ ክፍለ ከተማ 167 ተማሪዎች፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ ደግሞ 365 ተማሪዎች የነፃ ትምህርት ዕድሉ እንዲደርሳቸው ተደርጓል። የኮሮና ቫይረስ ከፍተኛ ጉዳት ካደረሰባቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የትምህርት ዘርፍ መሆኑን የተናገሩት ወይዘሮ ሸዊት፤ ይሁንና ችግሩ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ መንግሥት፣ የትምህርት ተቋማት አመራሮች እና መምህራን እንዲሁም ወላጆች በጋራ ውይይቶችን በማድረግ ይበጃል የሚሏቸውን አማራጮች በመከተል ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል። በዚህ ረገድ በማህበራዊ ሚዲያ፣ በኦንላይ እንዲሁም በቴሌቪዥን እና በሬዲዮ በሚተላለፉ ፕሮግራሞች አማካኝነት ትምህርቱ ለተማሪዎች እየደረሰ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህ ወቅት ደግሞ የግል ትምህርት ቤቶች የወላጆቻቸው ገቢ የቀነሰባቸውን ተማሪዎች በነፃ ለማስተማር ፍቃደኛ መሆናቸው የሚበረታታ ተግባር መሆኑን በመግለጽ ለበጎ ተግባሩም የግል ትምህርት ቤቶቹን በባለቤትነት የሚመሩ ባለሀብቶች እና የየተቋማቱ ኃላፊዎች ፍቃደኝነት አስፈላጊ እንደነበር ጠቁመዋል። በመሆኑም አርአያነት ላለው የየትምህርት ቤቶቹ በጎ ውሳኔ በባለሥልጣን መስሪያ ቤታቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ውስጥ 47 በመቶዎቹ የሚማሩት በግል ትምህርት ቤቶች ነው። በዚህም መሠረት ከ400ሺ በላይ ተማሪዎች በግል ትምህርት ቤቶች ውስጥ በተለያየ መንገድ የሚሰጡ ትምህርቶችን በመከታተል ላይ ናቸው።አዲስ ዘመን ግንቦት 3/2012 ጌትነት ተስፋማርያም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=32061
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c7006c6c8e146a4c234f36a539e4d0e9
f8d9293462abb276135264383fadbdd5
ከቤተሰቦቿ አምልጣ በካናዳ ጥገኝነት ያገኘቸው የሳዑዲዋ ወጣት ራሃፍ ሞሐመድ አል-ቁኑን ''የወሰድኩት እርምጃ አደገኛ ቢሆንም ትክክለኛ ውሳኔ ነው'' በማለት በካናዳ ነጻነት የሞላበት ህይወት እንደምትጀምር ተናግራለች።
ከቤተሰቦቿ አምልጣ ካናዳ የገባችው የሳዑዲዋ ወጣት፡ 'ምንም የሚጎልብኝ የለም'\nራሃፍ ሞሐመድ አል-ቁኑን ከሶስት ቀናት በፊት ካናዳ መግባቷ ይታወሳል የ18 ዓመቷ ወጣት ከቀናት በፊት ነበር ከቤተሰቦቿ ጋር በጉዞ ላይ ሳለች ወደ አውስትራሊያ ለማምለጥ በማሰብ ባንኮክ ከተማ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ እራሷ ላይ በመቆለፍ ወደ ሳዑዲ አልመሰም ያለችው። ራሃፍ በትዊተር ገጿ ላይ በምትለቃቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎች የእስልምና ሀይማኖትን መካዷን እና ወደ ሳዑዲ ብትመለስ ጨቋኝ ናቸው የምትላቸው ቤተሰቦቿ ሊገድሏት እንደሚችሉ የተናገረችው። • የሳዑዲ ሴቶች መሪ ጨበጡ • በሳዑዲ 'አንድ ወንድ እኩል ይሆናል ሁለት ሴት' • ሳዑዲ ሴቶች ወደ ስታዲየም እንዲገቡ ልትፈቅድ ነው የወሰድኩት እርምጃ አደገኛ እንደሆነ ይገባኛል ይሁን እንጂ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። ምንም የሚጎድልብኝ ነገር አይኖረም ስትል ቶሮንቶ ስታር ለተሰኘ ጋዜጣ ተናግራለች። ''የህይወት ታሪኬን እና የሳዑዲ ሴቶች የሚደርስባቸውን በደል በይፋ መናገር እፈልጋለሁ። እንደ እቃ ነው የምንቆጠረው፤ እንደ ባሪያ።'' ብላለች ራሃፍ። "ይህ ይሆናል ብዬ በጭራሽ አላሳብኩም ነበረ። የሰው ልጆች መብት በሚከበርባት ካናዳ ደህንነቴ እንደተጠበቀ ይሰማኛል።'' ስትልም ተናግራለች። ራሃፍ ከወላጆቿ ጋር ወደ ኩዌት እየተጓዘች ሳለ ነበር የአውስትራሊያ ቪዛ እንዳላት በመናገር በባንኮክ አድርጋ ወደ አውስትራሊያ ለመግባት ከወላጆቿ ያመለጠችው። ይሁን እንጂ ባንኮክ አየር ማረፊያ እንደደረሰች የሳዑዲ ዲፕሎማት ፓስፖርቴን ስለቀማኝ ጉዞዬን መቀጠል አልቻልኩም ብላ ነበር። ወንድሟና አባቷ ራሃፍን ወደ ሳዑዲ ለመመለስ ባንኮክ አየር ማረፊያ ድረስ ሄደውም ነበር። ራሃፍ ባንኮክ የሆቴል ክፍል ውስጥ እራሷ ላይ ቆልፋ፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና የተለያዩ ሀገራት መንግሥታት እንዲታደጓት ጥሪ አቅርባ ነበር። የወጣቷ ጉዳይ የበርካቶችን ቀልብ ስቦ ነበረ። የታይላንድ መንግሥት በባንኮክ እንድትቆይ ፍቃድ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን፤ የተባበሩት መንግሥታትም የጥገኝነት ጥያቄዋን ሲያስፈጽምላት ነበረ። ካናዳ ለራሃፍ ጥገኝነት በመስጠቷ ወጣቷ ከሦስት ቀናት በፊት ቶሮንቶ ገብታለች። በቶሮንቶ አውሮፕላን ማረፊያ የካናዳ የውጪ ጉዳይ ሚንስትርን ጨምሮ በርካታ ደጋፊዎቿ አቀባበል አድርገውላታል። ራሃፍ አል-ቁኑን የሚለውን የቤተሰብ ስሟን ከዚህ በኋላ እንደማትጠቀምበት አስታውቃለች።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
866738b8d550a1e363bdfe48964302d3
cd2788db880dadddb1ba7b0df7fbcd67
“የምንመለከተው ሁሉ የእኛ ስለመሆኑ ማረጋገጫ የለንምና ቀን ከሌሊት ሳንሰለች መከላከል ይጠበቅብናል፡፡” የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር ፋንታ ማንደፍሮ (ዶክተር)
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 04/2013ዓ.ም (አብመድ) በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ፋንታ ማንደፍሮ (ዶክተር) የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ቡድንም የበረሃ አንበጣ መንጋ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ተዘዋውረው አርሶ አደሮችን አነጋግረዋል፡፡ በተሁለደሬ ወረዳ የ027 ኮትቻ ቀበሌ አርሶ አደሮች ላለፉት 20 ቀናት ባደረጉት ዘመቻ ሰብላቸውን ከመንጋው መታደጋቸውን ተናግረዋል፡፡ሙሃመድ ይማም ቡሽራ እና ሁሴን አቡየ የቀበሌዋ ነዋሪ አርሶ አደሮች ናቸው፡፡ አርሶ አደሮቹ ላለፉት 20 ቀናት ከቤታቸው ወጥተው ውሎ አዳራቸው በማሳቸው አካባቢ ሆኗል፡፡ በተለያዩ አደረጃጀቶች ቦታ ተከፋፍለው የሚጠብቁት አርሶ አደሮቹ ከቀበሌያቸው አልፈው አጎራባች ዞኖች አና ወረዳዎች ድረስ ዘልቀው የመከላከል ሥራውን ይሠራሉ፡፡ “አንድ ጊዜ ወደ አካባቢው ከገባ በርትተን ብንከላከል እንኳን መጠነኛ ጉዳት ማድረሱ አይቀርም” ብለዋል አርሶ አደሮቹ፤ ከመግባቱ በፊት መከላከል ላይ ትኩረት እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡ መንጋው በሚገኝበት አካባቢ ከሌሊቱ 9፡00 ጀምረው ከወረዳ እና ቀበሌ የግብርና ባለሙያዎች ጋር በመሆን የኬሚካል ርጭት ያደርጋሉ፤ ቀን ቀን ደግሞ መግቢያ በሮች ናቸው ብለው በገመቷቸው አካባቢዎች ጭስ ያጨሳሉ፤ የመኪና ጎማ ያቃጥላሉ እንዲሁም ሌሎች ባህላዊ የመከላከያ መንገዶችን ሲጠቀሙ ይውላሉ፡፡ ይህ የአርሶ አደሮቹ ቀን ከሌሊት የአንበጣ መንጋውን ለመከላከል የሚያደርጉት ጥረት ነው፡፡ቀበሌዋም እስካሁን ድረስ እየተከሰተ ባለው የበርሃ አንበጣ መንጋ ጉዳት ያልደረሰባት እና እጅ ያልሰጠች ሆናለች፡፡ ሰብላቸው ተሰብስቦ ወደቤት እስኪገባ ድረስ ዘመቻው እንደሚቀጥልም አርሶ አደሮቹ ተናግረዋል፡፡ ኬሚካል መርጫ እና ሌሎች ግብዓቶችን በማሟላት መንግሥት ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል፡፡“የኮትቻ ቀበሌ አርሶ አደሮች ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች አጎራባች ዞን እና ቀበሌዎችም አርአያ ሆነዋል” ያሉት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ታደሰ ግርማ ናቸው፡፡ በዞኑ በአርጎባ፣ ተሁለደሬ እና ወረባቦ ወረዳዎች በሚገኙ 15 ቀበሌዎች የበረሃ አንበጣ መንጋው መከሰቱን አቶ ታደሰ ተናግረዋል፤ አርጎባ እና ተሁለደሬ ወረዳዎች እስካሁን ድረስ መንጋውን ሙሉ በሙሉ ሲቆጣጠሩ በወረባቦ ወረዳ 12 ቀበሌዎች ላይ ጉዳት ማድረሱን ገልጸዋል፡፡ በተሁለደሬ ወረዳ የታየውን መልካም ተሞክሮ ወደሌሎች ቀበሌዎች እና ወረዳዎች ለማስፋት እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ ለታየው በጎ ተነሳሽነትም አርሶ አደሮች፣ በየደረጃው ያሉ የሥራ ኃላፊዎች እና ግንባር ቀደም የግብርና ባለሙያዎች ሊመሠገኑ እንደሚገባ የግብርና መምሪያ ኃላፊው ገልጸዋል፡፡“ትናንት በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ባቲ ወረዳ ወዮ ፈላና ቀበሌ ተገኝቸ ተስፋ ቆርጨ ነበር” ያሉት የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር ፋንታ ማንደፍሮ (ዶክተር) “የእናንተ ጥረት እና ውጤት ደግሞ አሁንም ተስፋ እንዲኖረን ያደረገ ነው” ብለዋል፡፡ የተዘራው ሰብል እስካሁን ሳይወድም መቆየቱ ተአምር ሳይሆን የአርሶ አደሮቹ፣ የሥራ መሪው እና የግብርና ባለሙያዎች የተቀናጀ የልፋት ውጤት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ ዛሬ ባለው ተስፋ ሳይዘናጉ እስከመጨረሻው መረባበረብ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡ “የምንመለከተው ሁሉ የእኛ ስለመሆኑ ማረጋገጫ የለንምና ቀን ከሌሊት ሳንሰለች መከላከል ይጠበቅብናል” ነው ያሉት ምክትል ርእሰ መሥተዳድሩ፡፡ አርሶ አደሮቹ የጠየቁት ግብዓት በአፋጣኝ እንደሚደርሳቸው እና ከመንግሥት በኩል የበረሃ አንበጣ መንጋውን ለመከላከል ምንም የሚጎድል ነገር እንደማይኖር ቃል ገብተዋል፡፡ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው -ከተሁለደሬ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%a8%e1%88%9d%e1%8a%95%e1%88%98%e1%88%88%e1%8a%a8%e1%89%b0%e1%8b%8d-%e1%88%81%e1%88%89-%e1%8b%a8%e1%8a%a5%e1%8a%9b-%e1%88%b5%e1%88%88%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%91-%e1%88%9b%e1%88%a8/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
cb994c12a86bee0306f630179d33e817
39632b436fd43c7d942ac93a4fd845c0
ኢቫን ሳፍሮኖቭ ወታደራዊ ጉዳዮች የሚዘግብ ጋዜጠኛ ነበር። የሩስያ የደህንነት ተቋም ለቼክ ሪፐብሊክ ሚስጥራዊ መረጃ አቀብለሀል በሚል በቁጥጥር ስር አውሎታል።
ሩስያ ጋዜጠኞቿን የምታድነው ለምንድን ነው?\nሩስያውያን ጋዜጠኞች የታሰረበት ምክንያት “የማያሳምን” ነው ይላሉ። ኢቫን ፍርድ ቤት የቀረበው የፊጥኝ ታስሮ፣ አንገቱን አቀርቅሮ ነበር። ሁለት ጭምብል ያደረጉ ጠባቂዎች ኢቫን ቀና እንዳይል ይጫኑት ነበር። መናገር የቻለው “ንጹህ ነኝ” የሚል አረፍተ ነገር ብቻ ነበር። ፍርድ ቤቱ ውስጥ በርካታ ደጋፊዎቹ ተገኝተውም ነነር። የሩስያ ደህነት ተቋም ጋዜጠኛውን ለመያዝ የተጠቀመው የስለላ መንገድ በመንግሥት በኩል ቢመሰገንም፤ ኢቫን ለቼክ ሪፐብሊክ መረጃ ስለመስጠቱ የሚያሳይ ሰነድ ለሕዝብ ይፋ አለመደረጉ አነጋጋሪ ሆኗል። በሩስያ አገር በመክዳትና በስለላ ተጠርጥረው የሚታሰሩ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። ኢቫንም ከነዚህ አንዱ ነው ብለው ጓደኞቹ ይሰጋሉ። “ፑቲን ማንም ምንም ቢያስብ ግድ አይሰጣቸውም” ለመጨረሻ ጊዜ ሩስያ ውስጥ በአገር መክዳት ጋዜጠኛ የተከሰሰው በጎርጎሳውያኑ 1997 ላይ ነበር። ያኔ ለፍርድ ከቀረቡ አንዱ የሆነው ግሪጎሪ ፓስኮ፤ “20 ዓመታት ወደኋላ የተመለስኩ መሰለኝ” ይላል። ግሪጎሪ የወታደራዊ ጉዳየች ዘጋቢ ነበር። የሩስያ የባህር ጦር ጥሰት ስለመፈጸሙ በተደጋጋሚ ይጽፋል። ለጃፓን ሚስጥራዊ መረጃ በመስጠት ተከሶ ነበር። 2001 ላይ የአራት አመት እስራት ተፈርዶበታል። ፍርዱ በሩስያና ከሩስያ ውጪም ተቃውሞ አስነስቷል። ግሪጎሪም አራት ዓመት ሳይታሰር በድርድር ተፈቷል። “ከዛ በኋላ ጋዜጠኞችን መንካት ፈርተው ነበር። ያኔ ሩስያ የዓለም አቀፉ መዋቅር አካል ስለነበች ለሌሎች አገሮች አስተያየት ቦታ ይሰጡ ነበር። ቭላድሚር ፑቲን ለ20 ዓመታት ስልጣን ላይ ከቆዩ በኋላ ግን ስለማንም ሐሳብ ግድ የላቸውም” ይላል። ፕሬዚዳንቱ ለሁለት ተጨማሪ ዓመታት ለመግዛት ሕገ መንግሥቱን ማሻሻላቸውንም ግሪጎሪ ያጣቅሳል። “ምንም ገደብ የለም፤ የፈለጉትን ነገር፣ ባሰኛቸው ሰው ላይ፣ እንዳሻቸው መፈጸም ይችላሉ” ሲል ሁኔታውን ይገልጻል። መንግሥት ኢቫን የታሰረው ጋዜጠኛ ስለሆነ አይደለም ቢልም፤ ግሪጎሪ ግን አይስማማም። መንግሥት እንዲነኩበት የማይፈልጋቸውን ጉዳዮች በማንሳቱ እንደታሰረ ያምናል። “ጋዜጠኞች እጃቸውን እንዳያስገቡ ማስጠንቀቂያ ነው” ይላል። የስለላ ክስ በሩስያ ሩስያ ክሬሚያን በግዳጅ የግዛቷ አካል ማድረጓን ተከትሎ ከምዕራቡ ዓለም ጋር ያላት ግንኙነት ሻክሯል። ይህን ተከትሎም ከ2014 ወዲህ በስለላ ክስ የሚመሰርትባቸው ሰዎች ቁጥር ጨምሯል። 2013 ላይ ሦስት ሰዎች በአገር መክዳት ተከሰው ነበር። በቀጣዩ ዓመት ደግሞ 15 ሰዎች ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ከዛ በኋላ ቢያንስ 36 ተመሳሳይ ክሶች የተከፈቱ ሲሆን፤ 14 የውጪ አገር ዜጎችም በስለላ ክስ ተመስርቶባቸዋል። በየዓመቱ፤ ፑቲን የደህንት ሠራተኞቻቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰላዮችና የውጪ አገራት ተላላኪዎችን በማጋለጣቸው ያሞግሷቸዋል። እነዚህ ግለሰቦች ምን እንደሚደረጉ ግን አይገለጽም። የቀድሞው የኤፍኤስቢ ኃላፊ “አገራችን ውስጥ ያሉ የውጪ አገር ሰላዮች እንዳልቀነሱ የሚያሳይ መረጃ አለን” ብለው ነበር። ባለስልጣኖች አዳዲስ የውጊያ መሣሪያዎችንና ወታደራዊ ቴክኖሎጂን የተመለከተ መረጃ በጥንቃቄ እንዲይዙም አሳስበዋል። የሚታሰሩት ሰዎች እውን ሰላይ ናቸው? የጋዜጠኛው ኢቫን ጠበቃ ኢቫን ፓቭሎቭ እንደሚሉት፤ ከ2014 ወዲህ ሩስያ በየአቅጣጫው ካሉ ‘ጠላቶች’ ጋር ውጊያ ውስጥ ነን ትላለች። አገሪቱም በከፍተኛ ሁኔታ ወታደራዊ ሆናለች። ከዓመታት በፊት ጋዜጠኛውን ግሪጎሪ፣ አሁን ደግሞ ኢቫንን የወከሉት ጠበቃ፤ “በዚህ ጉዳይ ለዓመታት ስሠራ አንድም ሰላይ አጋጥሞኝ አያውቅም” ይላሉ። “ጠላቶችን መያዝ የኤፍኤስቢ ሥራ ነው። እውነተኛ ጠላት ካጡ መፍጠር ስላለባቸው ያገኙትን አካል ይከሳሉ” ይላሉ ጠበቃው። እሳቸው...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
913b43023b469892278969d690162ec2
954a3f406f9542dc9227d4ee412ac909
ትራምፕ የኢራቅ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአሜሪካ ወታደሮች አገሪቱን ለቅቀው እንዲወጡ የሚወስን ከሆነ ከባድ ማዕቀብ እንደሚጥሉ አስጠነቀቁ።
ትራምፕ ኢራቅ አይታ የማታወቀው ማዕቀብ ይጠብቃታል ሲሉ አስጠነቀቁ\nዶናልድ ትራምፕ ኢራቅን" አይተውት በማያውቁት መጠን ማዕቀብ ይጠብቃቸዋል" ሲሉ አስጠነቀቁ " እጅግ ውድና ግዙፍ የሆነ የአየር ኃይል ጦር ሰፈር [በኢራቅ] አለን። ለመገንባት ቢሊየን ዶላሮች አፍስሰንበታል። እስካልከፈሉን ድረስ ለቅቀን አንወጣም" በማለት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። አሜሪካ ኢራናዊውን የጦር አበጋዝ ከገደለች በኋላ በቀጠናው ውጥረት ነግሰዋል። • ኢራን ከዚህ በኋላ ለአሜሪካ ማዕቀብ እንደማትገዛ አስታወቀች • ቴህራን ጥቃት ከፈፀመች በሚል አሜሪካ 52 የኢራን ተቋማት ላይ መሳሪያዋን አነጣጥራለች • ኢራቃዊያን የጀነራሉን አስክሬን ሲሸኙ ''ሞት ለአሜሪካ'' ሲሉ ተደምጠዋል ኢራን የጄነራሏን መገደል "እበቀላለሁ" ስትል የዛተች ሲሆን እኤአ በ2015 ለፈረመችው የኒውክሌር ስምምነት እንደማትገዛም አስታውቃለች። የ62 ዓመቱ ሶሌይማኒ ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያላትን የጦር እንቅስቃሴ በበላይነት ይመሩ ነበር። አሜሪካ ለዚህ ተግባራቸው 'አሸባሪ' የሚል ስያሜ ሰጥታቸው ስትከታተላቸው መኖሯ ተዘግቧል። የጄነራሉ አስክሬን ወደ ኢራን የተወሰደ ሲሆን፣ በመገደላቸው የተቆጡና ሀዘናቸውን ለመግለጽ የወጡ ኢራናውያን የቴህራንን ጎዳናዎች አጨናንቀውት ታይተዋል። አዲሱ ጄነራሉን ተክተው የተሾሙት ግለሰብ፣ ኢስማኤል ቃኒ፣ አሜሪካን ከመካከለኛው ምስራቅ ጠራርገን እናስወጣታለን ሲሉ ዝተዋል። በሀገሪቱ የሬዲዮ ጣቢያ ላይ ቀርበው " ሶሌይማኒ የጀመረውን ለማስቀጠል ቃል እንገባለን። ለኛ ካሳ የሚሆነው አሜሪካ ተጠራርጋ ከመካከለኛው ምስራቅ ስትወጣ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል። ሶሌይማኒን የገደለው የአየር ጥቃት ኢራቃዊው ጦር ጄነራልንን፣ አቡ ማህዲ አል ሙሀንዲስ፣ ገድሏል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በአውሮፕላናቸው ውስጥ ሆነው ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ኢራቅ ከሀገሯ እንድንወጣ ከጠየቀች፣" አይተውት በማያውቁት መጠን ማዕቀብ እንጥልባቸዋለን። የኢራናውያኑ ማዕቀብ ምን አለውና" ብለዋል። አሜሪካ በኢራቅ ውስጥ 5000 ወታደሮች ያሏት ሲሆን ከኢራቅ ጦር ጋር በጋራ በመሆን አይኤስን ሲዋጉ ነበር። እሁድ እለት ጥምር ጦሩ እንቅስቃሴውን ለጊዜው ያቋረጠ ሲሆን የኢራቅ ህዝብ እንደራሴዎች የውጪ ኃይሎች ሀገሪቱን ለቅቀው እንዲወጡ የሚጠይቅ ህግ አርቅቀው ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። ኢራን በትናንትናው እለት ባወጣችው የአቋም መግለጫ እኤአ በ2015 የለፈረመችው የኑውክለር ስምምነት እንደማትገዛ ገልጻ፣ እንዳሻት እንደምትንቀሳቀስ አስታወቃለች። የኢራን ካቢኔ ዋና ከተማዋ ቴህራን ላይ ከመከረ በኋላ ነው አቋሙ የወጣው።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
84ae50cbfcb42f1caadabbe2196c6619
e7264b5b450b6beeee2aeb2064ae16bb
አሜሪካ 60 የሞስኮ ዲፕሎማቶችን ልታስወጣ ነው
አሜሪካ የአውሮፓ ሀገራት በሩስያ ዲፕሎማቶች ላይ የወሰዱትን እርምጃ በመከተል 60 የሞስኮ ዲፕሎማቶችን ልታስወጣ ነውአስቀድሞ 14 የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት የሩስያን ዲፕሎማቶች እንደሚያስወጡ፥ በህብረቱ ሀላፊ ዶናልድ ታስክ በኩል አስታውቀዋል፡፡በቀጣይም ሌሎች እርምጃዎችን እንደሚተገበሩ የህብረቱ ሀገራት በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው፡፡በእስካሁኑ ሂደት የጀርመን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አራት የሩስያ ዲፕሎማቶችን ማስወጣቱን ገልፆ፤ እርምጃው ለእንግሊዝ አጋርነትን ያሳየ መሆኑን አሳውቋል፡፡  ፖላንድና ፈረንሳይም የጀርመንን ውሳኔ በተመሳሳይ የተገበሩ ሲሆን ሉቲኒያና ቼክ ሪፑብሊክም እያንዳንዳቸው ሶስት ሶስት የሩስያ ዲፕሎማቶችን እናስወጣለን ብለዋል፡፡ለእንግሊዝ ትብብር ለማሳየት ውሳኔ ካሳለፉ ሀገራት መካከል  ዴንማርክ፣ ጣልያንና ኔዘርላንድ የሚጠቀሱ ሲሆን ሁለት ሁለት ዲፕሎማቶችን የማስወጣት ውሳኔ አሳልፈዋል፡፡በተጨማሪም ስድስት የአውሮፓ ህብረት ሀገራትም በተናጠል ለአንድ አንድ ዲፕሎማቶች የውጡልን ደብዳቤ አስተላልፈዋል፡፡እንደ ዋሽንግተን ሁሉ ዩክሬንም 13 ሩስያውያንን ውሳኔ የተመለከተ ዝርዝር አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ፔትሮ ፖሮሼንኮም የወሰድነው እርምጃ ከአውሮፓ ህብረት ሀገራት ጋር ያለንን ጥምረት ያሳየንበት ነው ብለዋል፡፡ሩስያ በመጪው ሰኔ ወር ለምታዘጋጀው የአለም ዋንጫ የአይስላንድ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የሀገሪቱ ባለስልጣናት ወደ ሞስኮ እንደማያቀኑ ገልጿል፡፡በዚህ ሁሉ ውርጅብኝ የሩስያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በዲፕሎማቶቻቸው ላይ ለተወሰደው እርምጃ አፀፋውን ለመመለስ ዘግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ቀደም ባለው ጊዜ ሞስኮ ዋሽንግተን ለምትወሰድው እርምጃ 60 ዲፕሎማቶችን እንደምታስወጣ ማስጠንቀቋን ዘገባው አስታውሷል፡፡አስካሁን ከየሀገራቱ እንዲወጡ ውሳኔ የተላለፈባቸው የሞስኮ ዲፕሎማቶች ቁጥር በድምሩ 100 ደርሷል፡፡በዚህ ውዝግብ እየተሳተፉ ያሉ ሀገራት ቁጥርም 23 መድረሱ ታውቋል፡፡ሩስያ በምዕራባውያን ያረፈባትን በትር በቀላሉ እንደማትመለከትና ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪዎቹ ጊዜያት የሚያስተላልፉት ውሳኔ ከሀገራቱ ጋር ባላት ግንኙነት ላይ ተመስርቶ እንደሚቀጥል የከሬምሊን ቃል አቀባይ ዲምትሪ ፔስኮቭን ተናግረዋል፡፡ (ሲ ጂ ቲ ኤን)
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/33811/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f539af244ff0f1f66cc1e039ef898551
4e435aa54bfb277fa2b53cdd7c782f9d
በቴክሳስ ከሃያ ሥድስት በላይ ሰው ሰለገደለው ወጣት
ዩናይትድ ስቴትስ ቴክሳስ ክፍለ ሃገር አንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተኩስ ከፍቶ ሃይ ሥድስት ሰው ገድሎ ሌሎች ከሃያ በላይ ያቆሰለው የሃይ ስድስት ዓመት ዕድሜው ዴቪን ኪሊ ጥቃቱን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳው የቴክሳስ ባልሥልጣናት ክትትል ይዘዋል።ከዩናይትድ ስቴትስ የአየር ኃይል በባህሪ ጉድለት የተባረረ ሰው መሆኑ ተገልጿል። የቴክሳስ ሀገረ ገዢ ግሬግ አበት ለሲቢኤስ ቴሌቭዥን በሰጡት ቃል የኃይለኝነት ዝንባሌ እና ችግር የነበረው ሰው እንደነበር ግልፅ ነው፣ ጊዜ ጠብቆ እንደሚፈነዳ ፈንጂ ነበር ብለዋል። ትናናት ረፋዱ ላይ ጥቃቱን ያደረሰው ኬሊ ከቤተክርስቲያኑ ጋር ግንኙነት የነበረው ይመስላል ብለዋል አገረ ገዢው።አማቾቹ ትናንት አልነበሩም እንጂ አልፈው አልፈው እዚያ ቤተክርስቲያን እንደሚያስቀድሱ ሀገረ ገዢው ጠቅሰው ይሄ የሚያሳየው ግለሰቡ ያገኘው ቦታ የከፈተው ጥቃት እንዳልሆነ ነው ብለዋል። በዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስቴር መረጃዎች መሰረት እኤአ ከ 2010 እስከ 2012 በአየር ኃይል ውስጥ አገልግለዋል በ2012 ሚስቱንና ልJune በመደብደብ አንድ ዓመት እሥራት ተፈርዶበት በኋላ ከጦር ኃይሉ እንዲሰናበት መደረጉ ተገልጿል።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/texas-shooting-11-6-2017/4102856.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c120eb3020adeab8331f5814d4afec84
732704555d6e823c33837419b1aec1c7
የትግራይ ክልል ምርጫ ነገ ይካሄዳል
የኢትዮጵያ መንግሥት ያልተቀበለውና በትግራይ ክልል ብቻ የሚካሂደው ምርጫ ነገ ጳጉሜ 4/2012 ዓ.ም ይካሄዳል።በምርጫው የሚሳተፉ አምስት ፓርቲዎች የትግራይ ህዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት አሳልፈን አንሰጥም በማለት በትናንትናው ዕለት በጋራ በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል።በዚህ የትግራይ ክልል ምርጫ ድምፅ ለመስጠት ከ2 ነጥብ 7 ሚልዮን በላይ መረጮች ተመዝግበዋል።።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/tigray-election-9-8-2020/5575678.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
6c2bb59fd0cd23d9fec78267fa664319
9c1cd4707897f56bc9f39234468a2d59
ምክር ቤቱ የኢትዮ-ጅቡቲ የተፈጥሮ ጋዝ ቧንቧ መስመር ዝርጋታ ስምምነትን አፀደቀ
አዲስ አበባ፣ታህሳስ 14፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢትዮጵያና በጅቡቲ መንግስታት መካከል የተፈጥሮ ጋዝ ቧንቧ መስመር ማስተላለፊያን ለመዘርጋት የተደረሰውን ስምምነት እና የፌዴራል ማረሚያ ቤት ረቂቅ አዋጆችን አፀደቀ።የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 7ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው እለት አካሂዷል።ምክር ቤቱ በዛሬው መደበኛ ስብሰባውም የፌዴራል ማረሚያ ቤት ረቂቅ አዋጅን ተመልክቷል።በዚህ ወቅት ከህግ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አቶ አበበ ጉዴቦ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፥ ቋሚ ኮሚቴው ረቂቅ አዋጁ ላይ ከፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግና ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጋር እንዲሁም ከህዝብ ክንፍ ጋር በቂ ውይይት መደረጉን አስታውቀዋል።ረቂቅ አዋጁ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የኢፌዴሪ ህገ መንግስት እና ህገ መንግስቱን መሰረት አድርገው የወጡ ህጎች እንዲሁም ሀገሪቱ ፈርማ ባፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች መሰረት እስረኞችን በመጠበቅ እና በማነፅ የተጣለበትን ሃላፊነት እንዲወጣ የሚያስችል መሆኑን አስታውቅዋል።እንዲሁም ረቂቅ አዋጁ የማረሚያ ቤቶችን አደረጃጀት የተሻለ ለማድረግ ፣የማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት ከተልዕኳቸው ጋር የሚመጣጠን የማረሚያ ቤት ፖሊስ የሚል ስያሜ አግኝተው ደረጃውን እና ሃላፊነቱን የሚገልፅ ማእረግ እና ምልክት እንዲኖራቸው የሚያደርግ መሆኑንም ገልፀዋል።በተጨማሪም ማረሚያ ቤቶች የእስረኞችን ሰብአዊ መብት በማክበር እንዲሁም የእስረኞቹ ግላዊ ሁኔታ በሚጠይቀው የፍርድ አፈጻጸም እና እርማት ስልቶችን ተግባራዊ በማድረግ እውቀትና ክህሎትን አዳብረው ከህብረተሰቡ ጋር የሚቀላቀሉበትን ስርዓት ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል።የምክር ቤቱ አባላትም የፌዴራል ማረሚያ ቤት ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያዩ በኋላ አዋጁን በሙሉ ደምጽ አጽድቀዋል።በመቀጠልም ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በጅቡቲ ሪፐብሊክ መንግስታት መካከል የተፈጥሮ ጋዝ ቧንቧ መስመር ለማስተላለፍ የተደረሰውን ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ተመልክቷል።ከተፈጥሮ ሀብት፣ መስኖና ኢነርጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ወይዘሮ ፈቲያ የሱፍ፥ ረቂቅ አዋጁ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ስምምነቱ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ጋዝ በሚዘረጋው ቧንቧ በማስተላለፍ ጋዙን ለሚጠቀሙ ሀገራት በመሸጥ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሚያስችላት መሆኑን ገልፀዋል።የቧንቧ መስመሩ ባለቤት ኢትዮጵያ መሆኗን በረቂቁ ላይ በግልፅ ፣ በሀገራቱ መካከል የተደረሰው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ መስመር ዝርጋታ ስምምነት ዓለም አቀፍ የስምምነት ደረጃ መስፈርትን የሚያሟላ እና ከዚህ በፊት በሀገራቱ መካከል የነበሩ ስምምነቶችን የሚያጠናክር መሆኑን ገልፀዋል።ይህንን ተከትሎም የምክር ቤቱ አባላት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በጅቡቲ ሪፐብሊክ መንግስታት መካከል የተፈጥሮ ጋዝ ቧንቧ መስመር ለማስተላለፍ የተደረሰው ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅን በሙሉ ደምጽ አፅድቀዋል።ምክር ቤቱ በመቀጠልም በውጭ ሀገራት ለተሰጡ የግልግል ዳኝነት ውሳኔዎች እውቅና የመስጠት እና የመፈጸም ስምምነትን ለማጽደቅ የቀረበ ረቀቅ አዋጅን ተመልክቷል።የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ደኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰጡት ማብራሪያ፥ የረቂቅ አዋጁ ዓላማ የግልግል ዳኝነት እና ስምምነት በአባል ሀገራት ፍርድ ቤቶች እውቅና እንዲኖራቸው እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረጉ ስምምነቶች የኢትዮጵያን ጥቅም የሚያስጠብቁ ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን እና የውጭ ሀገራት ኢንቨስትመንት እና ንግድን እንደሚያበረታታም አስረድተዋል።የምክር ቤቱ አባላትም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰጡት አስተያየት ኢትዮጵያ ስምምነቱን ብትቀበለው እና ብታፀድቀው በሀገሪቱ የሚሰጡ የግልግል ዳኝነት ውሳኔዎች በሌሎች ሀገራት ተፈፃሚ እንዲሆኑ እንዲሁም በሌሎች ሀገራት የተወሰኑ ውሳኔዎች በኢትዮጵያ እንዲፈፀሙ በማድረግ ነገሮችን ለማቀላጠፍ እና ለማቃለል እንደሚረዳ ገልፀዋል።ከአስፈፃሚ ጋር በተያያዘ በረቂቅ አዋጁ አስፈፃሚው ጠቅላይ አቃቤ ህግ ከሌሎች አካላት ጋር የሚለው ለምን በዝርዝር ለፖሊስ እና ፍርድ ቤት በሚል በግልፅ የሚል ጥያቄ የምክር ቤቱ አባላት አቀርበዋል።ምክር ቤቱም ረቂቅ አዋጁን ለዝርዝር እይታ በዋናነት ለህግ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም በተባባሪነት ለውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቷል።በሙለታ መንገሻ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%88%9d%e1%8a%ad%e1%88%ad-%e1%89%a4%e1%89%b1-%e1%89%a0%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab%e1%8a%93-%e1%89%a0%e1%8c%85%e1%89%a1%e1%89%b2-%e1%88%98%e1%8a%95%e1%8c%8d%e1%88%b5%e1%89%b3/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8638d3852bf4a9febb648b3a66032d0a
18ebf27a47eb5e1484da4c0671bc4eca
ኮማንድ ፖስቱ 11,607 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉ ይፋ ተደረገ
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሠረት የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት 11,607 ተጠርጣሪዎችን በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች አስሮ እንደሚገኝ ፓርላማው ያቋቋመው መርማሪ ቦርድ ይፋ አደረገ፡፡ፓርላማው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አፈጻጸምን እንዲመረምር ከፓርላማ አባላትና ከሕግ ባለሙያዎች የተውጣጡ ሰባት አባላትን የያዘ መርማሪ ቦርድ ማቋቋሙ የሚታወስ ሲሆን፣ ይኸው መርማሪ ቦርድ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የታሳሪዎችን ብዛትና ማንነት የማሳወቅ ሕገ መንግሥታዊ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡በዚሁ መሠረትም 11,607 ተጠርጣሪዎች በስድስት ማቆያዎች ታስረው እንደሚገኙ ኅዳር 2 ቀን 2009 ዓ.ም. ቦርዱ ይፋ አድርጓል፡፡ የመርማሪ ቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ታደሰ ሆርዶፋ ይፋ እንዳደረጉት፣ ከአጠቃላይ ተጠርጣሪ ታሳሪዎች ውስጥ የሴቶች ቁጥር 347 ነው፡፡የታሰሩባቸው ቦታዎችን አስመልክቶ ሲናገሩም በአዋሽ ማዕከል የታሠሩት 1,174 ተጠርጣሪዎች በዋናነት ከፊኒፊኔ፣ ከሰሜን ሸዋና ከምሥራቅ ሸዋ የተውጣጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በጦላይ የጦር ማሠልጠኛ 4,329 ተጠርጣሪዎች ተይዘው የሚገኙ መሆኑን በዋናነት የተያዙትም ከወለጋ፣ ከአርሲና ከምሥራቅ ሸዋ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡በዋናነት ከጉጂ፣ ከምዕራብና ከምሥራቅ ሐረርጌ የተያዙ 3,048 ተጠርጣሪዎች በዝዋይ መታሠራቸውን፣ 2,114 የሚሆኑ ሌሎች ተጠርጣሪዎች በዋናነትም ከጌዴኦ የተያዙ በዲላ ይርጋለም ማቆያ ታስረው እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡በባህር ዳር ማቆያ ማዕከል ደግሞ 532 ተጠርጣሪዎች እንደሚገኙ፣ እነዚህም በዋናነት የተያዙት ከሰሜንና ምሥራቅ ከጎንደር አካባቢ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተለያዩ ክፍላተ ከተሞች የተያዙ 410 ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ የተለያዩ ማቆያ ቦታዎች እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡የታሳሪዎቹን ማንነት በተመለከተም አብዛኞቹ ወጣቶች መሆናቸውን፣ በርካታ አርሶ አደሮችና ነጋዴዎች እንደሚገኙበት ነገር ግን ከ18 ዓመታት በታች የታሰረ አለመኖሩን ገልጸዋል፡፡መርማሪ ቦርዱ መረጃውን ያገኘው በራሱ አጣርቶ እንደሆነ የተጠየቁት አቶ ታደሰ፣ ኮማንድ ፖስቱ ለመርማሪ ቦርዱ ያቀረበው መረጃ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የእስረኞቹን አያያዝና ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ ከዚህ በኋላ ቦርዱ ማጣራት እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡እስረኞቹ የተጠረጠሩባቸው ወንጀሎች በርካታ ቢሆኑም ከዋና ዋናዎቹ መካከል ሁከት መፍጠር፣ ሰላም እንዳይኖር ሽብር መንዛት፣ የግለሰብ ቤት፣ የሕዝብና የመንግሥት ተቋማትን ማውደም፣ ማኅበራዊ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ በተለይም ግብይት እንዳይካሄድ የፀጥታ ኃይሎች ላይ ጥቃት ማድረስ፣ የመግደል ተግባር፣ ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማን መቅደድና ማቃጠል፣ ሕገወጥ መሣሪያ መሸጥ ተጠቃሽ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡የታሳሪዎቹ ዝርዝር ከቅዳሜ ኅዳር 3 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁሉም የክልል መንግሥታት እንደተላለፈና ክልሎችም ይህንን መረጃ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ እንዳለባቸው አስታውቀዋል፡፡ 
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%8A%AE%E1%88%9B%E1%8A%95%E1%8B%B5-%E1%8D%96%E1%88%B5%E1%89%B1-11607-%E1%89%B0%E1%8C%A0%E1%88%AD%E1%8C%A3%E1%88%AA%E1%8B%8E%E1%89%BD%E1%8A%95-%E1%89%A0%E1%89%81%E1%8C%A5%E1%8C%A5%E1%88%AD-%E1%88%A5%E1%88%AD-%E1%88%9B%E1%8B%8B%E1%88%89-%E1%8B%AD%E1%8D%8B-%E1%89%B0%E1%8B%B0%E1%88%A8%E1%8C%88
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b8b0db18b299aedd8d68d4af1340f6cd
54d14f49087806e71ecd9617430a74c5
“ወደ ፋሲል ያመራሁበት ምክንያቴ ዋንጫ ለማንሳት ነው” የዐፄዎቹ አዲስ ፈራሚ በረከት ደስታ
ተስፋ ከሚጣልባቸው ወጣት ተጫዋቾች መካከል ይጠቀሳል፡፡ በየጊዜው ፈጣን እና ሳቢ የእንቅስቃሴ ለውጦችን ከአዳማ ከተማ ከ20 ዓመት በታች ቡድን በ2009 ካደገ በኃላ በፕሪምየር ሊጉ እየደመቀ የመጣው የመስመር አጥቂው በረከት ደስታ በአዳማ ከተማ በዋናው ቡድን አራት ዓመታትን በማሳለፍ ለልጅነት ክለቡ በሚገባ ግሎጋሎትን መስጠት ችሏል፡፡ በክረምቱ ከአዳማ ከተማ ጋር ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ የአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ሀዲያ ሆሳዕናን ለመቀላቀል ቅድመ ስምምነት ፈፅሞ የነበረ ቢሆንም በፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት በመገኘት ፋሲል ከነማን በይፋ ተቀላቅሏል፡፡ለሁለት ዓመታት በክለቡ ለመቆየት ያመራው የመስመር አጥቂው ተከታዩን ሀሳብ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡“አዳማ በቆየሁባቸው አራት ዓመታት የተሻለ እና ጥሩ ጊዜን አሳልፌያለሁ። በታዳጊነቴ ስለገባሁም ደስ የሚሉ ቆይታዎችን አድርጊያለሁ። ሦስት ዓመት ቋሚ ሆኜ ተጫውቻለሁ። በአዳማ በነበረኝ ቆይታ ሁሉንም ማመስገን እፈልጋለሁ።“ፋሲልን በመቀላቀሌ ደስ ብሎኛል። ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ እና ጥሩ ከሚባሉት አንዱ ወደሆነው ቡድን በማምራቴ በውስጤ እጅግ ደስታን ፈጥሮልኛል። ፋሲልን በመቀላቀሌ ጥሩ ውሳኔን የወሰንኩ ያህል ይሰማኛል።“ሀድያ ሆሳዕና በእርግጥ ፈርሜ ነበር። ሆሳዕና እንደ የትኛውም ቡድን ጥሩ ቢሆንም ባለው ስብስም ሆነ ውጤት ፋሲል የተሻለ ነው። የተሻሉ ደጋፊዎች ያሉበት እና ጥሩ ጥሩ ነገሮች የሚገኙበት ክለብ ነው ብዬ ነው የገባሁት።“ፋሲል የገባሁበት ምክንያቴ ዋንጫ ለማንሳት ነው፡፡ እሱንም እናሳካለን ብዬ ተስፋ ስለማደርግ ነው። ራሴንም ለመፈተንም ጭምር ነው ልገባ የቻልኩት። ካለሁበት ክለብ ወደተሻለ ክለብ ገብቼ ራሴን ለመፈተሽ ፋሲልን ተቀላቅያለሁ። ሁለት የተሳኩ ዓመታት አሳልፋለሁ ብዬ አስባለሁ።”
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/60457
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
4c4bdfb31e5239e945c9086e6e890e5f
3633eb84bad8210913a549594d391faf
ደቡብ ኮሪያ ውስጥ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር በአንድ ቀን ውስጥ በእጥፍ ጨመረ
ባለስልጣናቱ እንዳሉት ከትናንት አርብ ጀምሮ ባለው መረጃ ዛሬ ቅዳሜ ብቻ 229 አዳዲስ በኮሮናቫይረስ የተጠረጠሩ ሰዎች ተገኝተው በተደረገው ምርምራ ቫይረሱ እንደለባቸው ተረጋግጧል። ይህም በአገሪቱ ያሉትን በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ 433 ከፍ አድርጎታል። የደቡብ ኮሪያ ምክትል የጤና ጥበቃ ሚኒስትር እንዳሉት የበሽታው ወረርሽኝ "አሳሳቢ የሆነ አዲስ ደረጃ ላይ ሰርሷል"። ባለስልጣናት እንዳረጋገጡት አዲሶቹ በበሽታው ከተያዙት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ በአገሪቱ ደቡብ ምሥራቅ በምትገኘው የዴጉ ከተማ ውስጥ በሚገኝ አንድ ሆስፒታልና የሐይማኖት ስፍራ ጋር የተያያዙ ናቸው። እስካሁን በበሽታው በደቡብ ኮሪያ ውስጥ ሁለት ሰዎች የሞቱ ሲሆን ቁጥሩም እየጨመረ ሊሄድ ይችላል የሚል ስጋት አለ። የበሽታው ምንጭ እንደሆነ የተጠረጠረው ሆስፒታል በሚገኝበት ዴጉ አቅራቢያ ያለው ቾንግዶ የተባለው አካባቢ ልዩ ቁጥጥር የሚደረግባቸው አካባቢዎች ተብለው ተለይተዋል። በዚህ የተነሳ በዴጉ ከተማ ያሉ ጎዳናዎችም ጭር ብለዋል። ደቡብ ኮሪያ ከ76 ሺህ በላይ በበሽታው የተያዙ ሰዎችና ከ2 ሺህ ሦስት መቶ በላይ ከሞቱባት ቻይና ቀጥሎ ከፍተኛው የተረጋገጠ የህሙማን ቁጥር ያለባት አገር ሆናለች። የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክትር የሆኑት ዶ/ር ቴድሮስ አድሐኖም እንዳሉት፤ አዲስ እየታየ ያለው የወረርሽኙ ስርጭት ፍጥነት እጅጉን አሳሳቢ ነው። በተለይ ደግሞ ደካማ የጤና አጠባበቅ ሥርዓት ባላቸው የአፍሪካ አገራት ውስጥ በሽታው ከተከሰተ የሚያስከትለው ቀውስ አሳስቧቸዋል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
d678fcf39f6211364f58197286b72380
3b21bb76f5ba8f6cb8b290cd6d1aab99
የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸው ያልተያዙ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ሳይውሉ አይቀሩም ተባለ
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን እስካሁን ድረስ የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸው በቁጥጥር ሥር ያልዋሉ ግለሰቦች ቢዘገይም ነፃ እንደማይሆኑ አስታወቀ፡፡ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔነራል እንደሻው ጣሰው ሐሙስ የካቲት 14 ቀን 2011 ዓ.ም. በኮሚሽኑ መሥሪያ ቤት በሰጡት መግለጫ፣ የእስር ትዕዛዝ ለወጣባቸው ግለሰቦች ትዕዛዙን ለማድረስ ሲኬድ ያጋጠሙ ችግሮች እንደነበሩ በመግለጽ፣ በእንደዚህ ዓይነት ወቅት መታኮስ አስፈላጊ ስላልነበር የተለያዩ አማራጮች ላይ ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል፡፡‹‹አንዳንድ ጉዳዮች በመደበኛ የፖሊስ ሥራዎች ብቻ የሚፈቱ አይደሉም፡፡ የተለያዩ ቦታዎች ሔደው የተደበቁ ሰዎች አሉ፡፡ የእስር ማዘዣ ከወጣባቸው በኋላም የእስር ማዘዣውን ቦታው ድረስ ሄዶ ለመስጠት ሲሞከር ያጋጠሙ እንቅፋቶች አሉ፡፡ በዚህ ወቅት አትታኮስም፡፡ ሁኔታው አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ በጥሞና እንዲታይ ይደረጋል፡፡ ይኼ ለሰላም ሲባል ነው፡፡ ይኼ የሚደረገው አጠቃላይ ነገር እንዳይበላሽና እንዳይደፈርስ ሲባል ነው፡፡ ይኼ ማለት ግን ሄዶ ሄዶ የእስር ማዘዣ የወጣባቸው ሰዎች ነፃ ይወጣሉ ማለት አይደለም፡፡ እንኳን በአገር ውስጥ ያለ ይቅርና በውጭ አገር በወንጀል የተጠረጠረ ካለ ይዘን እናቀርባለን፤›› ሲሉም አብራርተዋል፡፡ይኼንንም ለማስፈጸም ከተለያዩ ክልሎች ጋር አስተዳደራዊ ውይይቶች እንደተደረጉ በማስታወቅ፣ ‹‹ጉዳዮቹ ጊዜ ተሰጥቷቸው የክልል መንግሥታትም የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ ይደረጋል፤›› ብለዋል፡፡ይሁንና በወንጀል የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን ይዘው የሚያስረክቡ ክልሎች እንዳሉም ያወሱት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፣ በተቃራኒው የሚደብቅ፣ የሚሸሽግና አካባቢዬ ላይ ተጠርጣሪው የለም ብሎ የሚያብር ሰው መልካም ተሞክሮ እንዳልሆነ፣ ብሎም የተጀመረውን ለውጥ የሚያናጋና የሚያበላሽ እንዲሁም የወንጀል መከላከል ሥራ ላይም ጥላ የሚያጠላ ጉዳይ ስለሆነ በሚታረምበት መንገድ ይታረማል ሲሉም አሳስበዋል፡፡
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/14864
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
228af2a66d48ee31a91b1c973a722537
2ff59f7839cc2a5285eb15994d2df892
አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ያልተያዙ ተከሳሾች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ትዕዛዝ ተሰጠ
አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ባልተያዙ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተከሳሾች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ ኢንዲደረግላቸው ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡በዚህም መዝገብ 26 ተከሳሾች ያሉ ሲሆን፣ አቃቢ ህግ የሚያቀርበውን የሰው ምስክር ለመስማት ሐምሌ 18፣ 23፣ 24፣ 25 እና 30/2011 ዓ.ም ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ከዚህ በፊት አቃቢ ህግ ለምስክሮቹ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ያቀረበው ማመልከቻ የምስክሮችን አድራሻ ባለመጥቀሱ አሻሽሎ ኢንዲያቀርብም ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡የጋዜጣ ጥሪ ውጤቱንና ተሻሽሎ የሚቀርበውን የምስክሮች ጥበቃ አቤቱታ ለመጠባበቅ ችሎቱ ለሐምሌ 9/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡በሌላ በኩል በቀድሞ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሃመድ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል አብዲኑር መሀመድ፣ ኮሚሽነር አብዱላሂ አህመድና ወይዘሮ ዘምዘም ሀሰን ማንነታቸውን የሚያረጋግጥላቸውን ማስረጃ ባቀረቡት መሰረት ሰኔ 2010 ዓ.ም ጀምሮ በሶማሌ ክልል ዘርንና ኃይማኖትን ለይቶ በተፈጸመው ጥቃት ላይ የነበራቸውን ሚና የሚያስረዳ ክስ ተነቦላቸዋል፡፡ከዚህ ቀደም ሻምበል አይድድ በደል በሚል አቃቢ ህግ ክስ የመሰረተባቸው ተከሳሽ ምክትል ኢንስፔክተር አይድድ ራጊ መሆናቸውን የሚያስረዱ ሰነዶች ዛሬ በዋለው ችሎት ያቀረቡት ማስረጃ ተቀባይነት አግንቷል፡፡ተከሳሹን በተመለከተ አቃቢ ህግ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከሌሎች ተከሳሾች ጋር ስማቸውን አሻሽሎ ማምጣቱ በችሎቱ ተነቅፏል፡፡ አቃቢ ህግም ይቅርታ ጠይቋል፡፡ ነገር ግን ለተከሳሹ ጥቅም ሲባል ተለዋጭ ቀጠሮ ከመስጠት ክሱን ማንበብ ተገቢ በመሆኑ በችሎቱ ክሳቸው ተነቦላቸዋል፡፡እስከ ሰኔ 20/ 2011 ዓ.ም ድረስም መቃወሚያቸውን እንዲያቀርቡና አቃቢ ህግም ምላሽ እንዲሰጥበት ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡በዚህ የክስ መዝገብ ከድር አብዲ እስማኤል የተባለ ግለሰብ የተያዘ ቢሆንም ስለስራ ድርሻው በክሱ የመንግስት የስራ ኃላፊ የሚል ቢሆንም፤ ግለሰቡ  ግን ገበሬ መሆኑን ለችሎቱ አስረድተዋል፡፡አቃቢ ህጉም ለችሎቱ  አቶ ከድር አብዲ እስማኤልን የሚፈልጋቸው ግለሰብ አለመሆናቸውን በማረጋገጡ፤ ችሎቱ በዛሬው ዕለት እንድለቀቅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/31195/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b723e4cba004fb0aa93c07451d4f24af
c914d97d313dec3d8d45a4b192a79da5
ለህዳሴ ግድብ ግንባታ መዘግየት ምን አይነት መፍትሔዎች እየተሰጡ ነው?
ነገር ግን ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በሁለት አጋጣሚዎች የህዳሴው ግድብ ከመቼውም የበለጠ መነጋገሪያ ሆኗል። በመጀመሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እስካሁን እየሄደ ባለበት ፍጥነት ግድቡ በመጭው አስር ዓመትም አይጠናቀቅም ብለዋል የሚል መረጃ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በብዛት መንሸራሸሩን ተከትሎ ግድቡ የሁሉም መነጋገሪያ ሆነ። ከዚያ ደግሞ የግድቡ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑትና የግድቡ ምልክት ተደርገው የሚወሰዱት ኢንጅነር ስመኘው በቀለ ግድያ የግድቡ ጉዳይ ብዙዎችን አነጋገረ፣ አሳሰበም ጭምር። •ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ሕይወታቸው ያለፈው በጥይት ተመተው ነው፡ ፌደራል ፖሊስ •ስለኢንጂነር ስመኘው አሟሟት እስካሁን ምን እናውቃለን? •የኢንጂነር ስመኘው ቤተሰቦች የምርመራው ውጤት በምንፈልገው ፍጥነት እየሄደ አይደለም አሉ በኢንጅነር ስመኘው ህልፈት ማግስት መግለጫ የሰጡት የውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሃይል ሚኒስቴሩ የህዳሴው ግድብ የሲቪል ኢንጅነሪንግ ክፍሉ ግንባታ በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ ቢሆንም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ ክፍሉ ማለትም የጀነሬተርና ተርባይን ተከላ ስራ መዘግየቱን ገልፀው ነበር። ሌላው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ ክፍል ውስጥ ያለው የማመንጫ ጣቢያ ነው። በግድቡ ግንባታ ሂደት ላይ ችግር የሆነ ነገሮችን መፍታት የሚያስችሉ እርምጃዎችን እየተመለከቱ መሆኑንም አመልክተው ነበር። ከጥቂት ቀናት በፊት ደግሞ ግድቡ በተያዘለት የግንባታ ሂደት እየተከናወነ መሆኑን የገለፁትን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አዜብ አስናቀን የግድቡ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ክፍል ከመዘግየቱ አንፃር አሁን የግድቡ ግንባታ ምን ላይ ነው ስንል ጠይቀናቸው ነበር። "ግንባታው በአንድ ሰው ላይ ሳይሆን አሰራር(ሲስተም)ላይ የተመሰረተ ስለሆነ ሌላ ሰው ሃላፊነት ይረከባል ስራውም ይቀጥላል እየቀጠለም ነው"በማለት የግንባታው የዘገዩ ስራዎች መኖራቸውን ነገር ግን ይህ የተለየ ሳይሆን በዓምስት ተብሎ በአስር ዓመት እንደሚጠናቀቁ የመንገድም ይሁን የሃይል ፕሮጀክቶች እንደሆነ በመግለፅ መልስ ሰጥተዋል። ፕሮጀክቶች ለምን ይዘገያሉ ለሚለው ክፍያን ጨምሮ የተለያየ ምክንያት ይቀመጣል።በህዳሴው ግድብም ተመሳሳይ ነገር መከሰቱን ተናግረዋል። የህዳሴው ግድብ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ ሂደቶች ተቀባብተው(ኢንተርፌስ አድርገው) ነው መሰራት ያለባቸው። ብረታ ብረቱ ሲሰራ ኮንክሪቱ ይቀጥላል።ኮንክሪቱ ሲሰራ ብረታ ብረቱ ይቀጥላል።እንደዚ እንደዚ እያለ ነው የሚሄደው። የግድቡን ግንባታ ችግር ለመፍታት መፍትሄ የተባለው ስፔሻላይዝ ያደረጉ ሰብ ኮንትራክተሮችን ማስገባት ሲሆን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራውን የሚያግዝ ተቋራጭ በማስገባትም የግድቡን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ክፍል ግንባታ ችግር ለመፍታት እየተሞከረ እንደሆነ ኢንጅነር አዜብ ያስረዳሉ። እንደ አውሮፓውያን በቀጣዩ ወር ሁለት ተርባይኖች ሃይል ማመንጨት እንዲጀምሩ እቅድ እንደነበር ከዚህ ቀደም መዘገቡን በማስመልከት ጥያቄ ያነሳንላቸው ኢንጅነር አዜብ እንደዚህ ያሉ ነገሮች ላይ እርግጠኛ ሆኖ መናገር ከፕሮጀክቱ ውስብስብ ተፈጥሮ አንፃር ከባድ እንደሆነ ያስረዳሉ። "ፕሮጀክቱ በጣም ውስብስብ ነውና ይህ በዚህ ጊዜ ለማለት ይቸግራል።ከዚህ አንፃር መስከረም ላይ ይሄ ይሆናል አይሆንም ማለት አይቻልም።ነገር ግን የመጀመሪያዎቹ ሁለት ዩኒቶች ስራ ጀምረው ሃይል እንዲያመነጩ የተለያዩ የማፋጠን እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው"ይላሉ። ሳሊኒ በግንባታ መዘግየት ለደረሰበት ኪሳራ ካሳ የመጠየቁ ነገር እየተሰማ ሲሆን የዚህ አይነቱ የተቋራጮች የካሳ ጥያቄ የሚጠበቅ ነው ይላሉ ኢንጅነሯ። ጊቤ ሶስት እንዲሁም ገናሌ ደዋሌን በምሳሌነት በመጥቀስም የኮንትራክተሮች...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
a59596700014975246db2c96a6879879
dd4d68a18449fc35a809e00e9b095d08
የኢራቅ ኃይል በእስላማዊ ቡድን ቁጥጥር ሥር የነበሩ ሥፍራዎች ለማስለቀቅ ጥቃት ከፍቷል
የኢራቅ ኃይል የኢራቅ ወታደራዊ ኃይል “እስላማዊ መንግሥት ነኝ” በሚለው ፅንፈኛ እስላማዊ ቡድን ቁጥጥር ሥር ያሉትን የመጨረሻ ቦታዎችን ለማስለቀቅ ጥቃት ከፍቷል።የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይዳር አል አባዲ አል ኳምና ራካ ላይ የቀሩት የፅንፈኛው ቡድን ጂሐዳውያን ያላቸው አማራጭ “ሞት ወይም እጅ መስጠት ነው” ሲሉ ዛሬ የጥቃቱን መከፈት አስታውቀዋል።የኢራቅ ሃይሎች ፅንፈኛው ቡድን ከሦስት ዓመታት ወዲህ ከተቆጣጠራቸው ግዛቶች ከ90 ከመቶ በላይ የሚሆኑትን የኢራቅ ወታደራዊ ኃይል ማስለቀቁ ታውቋል። የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ ኃይል እንደሚለው 1,500 የሚሆኑ የዳዕሽ አማፅያን አል ኩዋም አካባቢ ቀርተዋል።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/iraqi-military-takes-on-is-in-last-big-fights-10-26-2017/4087435.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3b457d9d33fdff1bfad238cbb1b310ea
9e19885baa3fe117205d6592b797e903
ለሁለት ወጣቶች ህልፈት ምክንያት የሆነው የቦታ ውዝግብ እንዲጣራ ተወሰነ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የቤተ ክርስቲያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስ በተለምዶ 24 ቀበሌ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ከቤተ ክርስቲያን የቦታ ጥያቄ ጋር በተያያዘ የተፈጠረው ችግር ከስረ መሠረቱ ከሶስት አካላት በተውጣጣ ኮሚቴ እንዲጣራ ተስማሙ፡፡የከተማ አስተዳደሩ ም/ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ የካቲት 12 ቀን 2012 ዓ.ም ከቅዱስ ሲኖዶስ ጋር በጉዳዩ ላይ ባደረጉት ውይይት ለሁለት ወጣቶች ሞት ምክንያት የሆነው የቦታ ውዝግብ ከአካባቢው ሽማግሌዎች፣ ከቤተ ክርስቲያኒቱና ከመንግሥት አካል በተውጣጣ የጋራ ኮሚቴ እንዲመረመር ተስማምተዋል፡፡ የተቋቋመው የጋራ አጣሪ ኮሚቴውም በቀጣይ 10 ቀናት ውስጥ ችግሩ እንዴት እንደተፈጠረ? ችግሩን መጀመሪያ የነበረውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ንዋየ ቅዱሳት ሁኔታ እንዲሁም ስለቦታው በዝርዝር አጥንቶ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይጠበቃል ሲሉ ምንጮች ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡ ከዚህ የቦታ ውዝግብ ጋር በተያያዘ ታስረው የነበሩ የአካባቢው ወጣቶችና የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ከእስር እንዲለቀቁም ስምምነት ተደርሷል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ቀደም ባለው ሳምንት ባካሄደው ልዩ ጉባኤው ቦታው የሁለት ክርስቲያን ወጣቶች ደም የፈሰሰበት እንደመሆኑና ቤተ ክርስቲያኒቱ በቦታው ላይ ቀደም ብላ ጥያቄ አቅርባ የነበረ በመሆኑ ቦታው ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሊሰጥ ይገባል ማለቱ ይታወሳል፡፡   
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=25051:%E1%88%88%E1%88%81%E1%88%88%E1%89%B5-%E1%8B%88%E1%8C%A3%E1%89%B6%E1%89%BD-%E1%88%85%E1%88%8D%E1%8D%88%E1%89%B5-%E1%88%9D%E1%8A%AD%E1%8A%95%E1%8B%AB%E1%89%B5-%E1%8B%A8%E1%88%86%E1%8A%90%E1%8B%8D-%E1%8B%A8%E1%89%A6%E1%89%B3-%E1%8B%8D%E1%8B%9D%E1%8C%8D%E1%89%A5-%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B2%E1%8C%A3%E1%88%AB-%E1%89%B0%E1%8B%88%E1%88%B0%E1%8A%90&Itemid=180
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c3d02e672e00916b533d905520cc4c21
4b8b615a788e60ebbfe1010738edb216
ቅዝቃዛው ጦርነት
«ቅዝቃዛው ጦርነት» ከሁለተኛ ዓለማዊ ጦርነት በኋላ በተለይ ከአሜሪካና ሶቪዬት ሕብረት መካከል የነበረው መቀያየም ይገልጻል። ከ1937 እስከ 1982 ዓም ድረስ ያለው ዘመን ነው። እነዚህ ሁለት ኃይለኛ አገራት መቸም «የሞቀ ጦርነት» ስላልነበራቸው ዘመኑ «ቅዝቃዛው ጦርነት» በመባል ታውቋል። እንዲያም ሁለቱ የኑክሌር መሣሪያ ሃያላት በመሆናቸው ጦርነቱ «የሞቀ» ከሆነ እንደ ሆነ «እርግጠኛ እርስ በርስ መጥፋት» ይሆን ነበር። የተረፈው አለም ወይም ከአንድ ወይም ከሌላው ወገን ወዳጅ ስለ ሆነ የአለም መጥፋት ማለት ነበር። ሁለቱ አገራት ግን በዛቻ፣ በሰላይ፣ በሴራ፣ በወኪል ጦርነት ይታገሉ ነበር። በተለይ አሜሪካ በቬትናም ጦርነት፣ በኋላም የሶቭየት ኅብረት በአፍጋኒስታን ጦርነት ተዋጉ። የቅዝቃዛው ጦርነት ዘመን በሶቭየት ኅብረት ውድቀት በ1982 ዓም ያህል ጨረሰ። ፖለቲካ ታሪክ የአሜሪካ ታሪክ
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
e400ffe003d671d28502ac41fec57276
40f483b9358cb1af9fbe9c5d27a9f004
በምሥራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ከተማ ደኅንነቱ ባልጠበቀ ሁኔታ ግንባታ ሲካሄድ በደረሰ አደጋ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ።
በአዳማ ከተማ ከግንባታ ጋር በተያያዘ አደጋ 4 ሰዎች ሞቱ\nአደጋው ያጋጠመበት ስፍራ የአዳማ ከተማ ኮሚኒኬሽን ጸ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ራውዳ ሁሴን ለቢቢሲ እንደተናገሩት በግንባታ ስፍራ የደረሰው አደጋ ሕይወታቸው ካለፈው 4 ሰዎች በተጨማሪ ሁለት ሰዎች ላይም ከፍተኛ የአካል ጉዳት አስከትሏል። ይህ አደጋ የተከሰተው ኢሬቻ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ነው። በስፍራው አንድ አሮጌ ቤት ፍርሶ አዲስ ሕንጻ እየተገነባ ነበር። አሮጌው ቤት ግን ሙሉ በሙሉ እንዳልፈረሰ ተጠቁሟል። የአሮጌው ቤት ግድግዳ እንደ አጥር ሆኖ ሲያገለግል ነበር። ይህ እንደ አጥር ሆኖ ሲያገለግል የነበረ የአሮጌ ቤት ግድግዳ ተደርምሶ ነው በቀን ሰራተኞች ላይ ጉዳቱን ያስከተለው ሲሉ ወ/ሮ ራውዳ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የጸ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ራውዳ ግንባታው ከመጀመሩ በፊት የአሮጌው ቤት ግድግዳ ሙሉ በሙሉ መፍረስ ነበረበት ብለዋል። የዓይን እማኞችን ምን ይላሉ? በግንባታ ስፍራው በቀን ሰራተኝነት የሚሠራው ኢብሳ አያና የተመለከተውን እንዲህ ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል። "ግድግዳውን ለማፍረስ ከስር ቦርብረውት ነበር። ከዛ መልሶ እነሱ ላይ ተደረመሰ። እኛ ሰባተኛ ፎቅ ላይ ነበረን። ጩኸት ሰምተን ስንወርድ እለያቸው ላይ ተደርምሷል" ኢብሳ እንደሚለው ሠራተኞቹን ከፍርስራሹ ስር ለማውጣት ረጅም ሰዓት ወስዷል። ግንባታው በሚካሄድበት ስፍራ ነዋሪ እንደሆነች የምትናገረው አስናቁ ደቻሳ ደግሞ ከፍርስራሹ የአራት ሰዎች አስክሬን ሲወጣ መመልከቷን ትናገራለች። "ሲደረመስ አይቻለሁ" የምትለው አስናቁ በአካባቢው በርካታ ሰዎች በለቅሶ ሐዘናቸውን ሲገልጹ ነበር ብላለች። በአደጋው ሕይወታቸው ያለፈው አራቱም የቀን ሠራተኞች ወንዶች መሆናቸው ተነግሯል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
c7337d7b655434f36d5b9e6e9e1151be
690b0c9248e53a5eba7ac2cc8ec45c92
ትራምፕ በማኬይን ቀብር ላይ አይገኙም
በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ጆን ማኬይን በቪየትናም ጦርነት ላይ የጦር አውሮፕላን አብራሪ በመሆን ሃገራቸውን አገልግለዋል። በአውሮፓውያኑ 2008 ላይ በተካሄደው የአሜሪካ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ከባራክ ኦባማ ጋር የተፎካከሩት ማኬይን ለሚቃወሟቸው ሁሉ የሚታገሉ ተብለው ይገለፃሉ። አቶ በረከት ስምኦን ከብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴ አባልነት ታገዱ የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውን አስከፊ ሁኔታ ላይ መሆናቸው ተገለፀ የመዋቢያ ምርቶች ውስጥ መርዛማ ንጥረ-ነገሮች ተገኙ ኦባማ «ከማኬይን ጋር ያሳለፍነው ጊዜ በቃላት የሚገለፅ አይደለም» ሲሉ ሰውየውን አሞግሰዋቸዋል። ጆርጅ ቡሽ በበኩላቸው «እርሱ እኮ የከፍተኛ ዓላማ አርበኛ ነበር» በማለት ነው ያንቆለጳጰሷቸው። በማኬይን ክፉኛ ወቀሳ ሲደርስባቸው የነበሩት የወቅቱ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በሰውየው ማለፍ የተሰማቸውን ሃዘን በመግለፅ ሃሳባቸውን ቋጭተዋል። የትራምፕ ባለቤት ቀዳማዊ እመቤት ሜላኒያ ትራምፕ በበኩላቸው «ለሃገራችን ላበረከቱት እናመሰግናለን» ሲሉ ከባላቸው በሃሳብ ላቅ ያለ ፅሑፍ አስፍረዋል። እንደ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ከሆነ ዶናልድ ትራምፕ በማኬይን ግብዓተ መሬት መርሃ ግብር ላይ እንዲገኙ አልተጋበዙም። በምትካቸው ምክትል ፕሬዝደንት ማይክ ፔንስ ሊገኙ እንደሚችሉ ነው መገናኛ ብዙሃኑ እየጠቆሙ ያሉት። በተቃራኒው የቀድሞዎቹ ባራክ ኦባማና ጆርጅ ቡሽ በዝግጅቱ ላይ ንግግር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል። በአይምሮ እጢ ምክንያት ለአንድ ዓመት ያህል በህክምና ሲረዱ የቆዩት የ81 ዓመቱ ማኬይን ህክምና በቃኝ በማለታቸው ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉን ቤተሰባቸው አስረድቷል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
f32a0b2e9194c608fa6f56c554460748
48e3b073e9e7fdb32c90847183ad852a
ተበላ! ጀርመን በላችው!
ጀርመን አርጀንቲናን በፍፃሜ ግጥሚያ ለሁለተኛ ጊዜ ድል ነሣች፡፡ ጨዋታው በተጨማሪ የጨዋታ ጊዜ በተቆጠረች ግብ አንድ ለባዶ አለቀ፡፡በሪዮ ዴ ጃኔይሮው ማራካና ስታዲየም የተካሄደው ጠንካራ ሊባል የሚችል ትንቅንቅ የታየበት ጨዋታ ዋናው የግጥሚያ ጊዜ /ዘጠና ደቂቃው/ የተጠናቀቀው፣ ብዙ የግብ አጋጣሚዎች ተፈጥረው የነበረ ቢሆንም፣ ያለምንም ግብ ባዶ ለባዶ በሆነ ውጤት ነበር፡፡ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰዓት ዘልቆ 112 ደቂቃ ከ21 ሰከንድ ላይ 19 ቁጥር ለብሶ የሚጫወተው ማሪዮ ግዮትዘ በድንቅ አስተላለፍ የአርጀንቲናን በረኛ አሳልፎ መረብ ላይ ያስቀመጣት ኳስ የጨዋታውም ለብርቱው የጀርመን ቡድንም በዚህ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያዋም የመጨረሻዋም ግብ ሆነች፡፡ጎ............................ል! ጀርመን የዓለም ዋንጫን ለአራተኛ ጊዜ ወሰደች፡፡በዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ታሪክ ጀርመን 4 ጊዜ አሸንፋ አምስት ጊዜ ያሸነፈችውን ብራዚልን እየተከተለች ነች፡፡በዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ታሪክ ውስጥ እአአ በ1954 ዓ.ም ልክ የዛሬ ስድሣ ዓመት ስዊትዘርላንድ አዘጋጅታው በነበረው 5ኛው የዓለም ዋንጫ ላይ ጀርመን ሃንጋሪን 3 ለ 2 አሸንፋ የመጀመሪያውን ዋንጫዋን ወስዳለች፡፡ከዚያም እአአ በ1974 ዓ.ም እራሷ /የያኔዋ ምዕራብ ጀርመን/ አዘጋጅታው በነበረው 10ኛው የዓለም ዋንጫ ላይ ለፍፃሜ ከሆላንድ ጋር ተገናኝታ 2 ለ 1 አሸነፈች፡፡እአአ በ1990 ዓ.ም /የዛሬ 24 ዓመት/ ጣልያን ባዘጋጀችው 14ኛው የዓለም ዋንጫ ልክ እንደዛሬው ጀርመንና አርጀንቲና ተገናኝተው፤ ልክ እንደዛሬው ጀርመን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋ ዋንጫውን አስቀረች፡፡ዛሬ፣ ዕሁድ - ሐምሌ 6/2006 ዓ.ም /በኢት.የዘ.አቆ/ የሪዮ ዴ ጃኔሮው ማራካና ስታዲየም ላይ ጀርመን የዛሬ ሃያ አራት ዓመቱን ታሪክ ደገመች፡፡የማርዮ ግዮትዘን ጎል ለማየት ከታች የተቀመጠውን ማገናኛ ይጫኑና ይከተሉ፤
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/1956721.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
31ed99fb7438e248943539b65fa38049
fe98b120610bcbc04ec87ae9f1001978
ኢጋድ ሊብያ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመውን ግድያ አወገዘ
እራሱን አይ ኤስ እያለ የሚጠራው አሸባሪ ቡድን ሊብያ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ የፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) አወገዘ።የኢጋድ ዋና ጸሐፊ አምባሳደር እንጂነር ማህቡብ ማአሊም ዛሬ እንደገለጹት ሊብያ ውስጥ  በንጹሃን ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን አሰቃቂና ትርጉም የለሽ ግድያ ድርጅቱ በጽኑ ያወግዛል።“ኑሮዋቸውን ለማሻሻል ሲሉ በአሰቃቂ ሁኔታ በአሸባሪው ቡድን በታረዱት ኢትዮጵያውያን አዝነናል። በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር አብረን እንቆማለን” ሲሉ ዋና ጸሐፊው ተናግረዋል።እራሱን አይ ኤስ እያለ የሚጠራው አሸባሪ ቡድን የእስልምና ሃይማኖትን አይወክልም ያሉት አምባሳደር እንጂነር ማአሊም በመላው አለም የሚገኙ ህዝቦች በአንድ ድምጽ ሊያወግዙት ይገባል ብለዋል።“የእስልምና ሃይማኖት ሰላማዊ ሃይማኖት ነው። የእስልምና ሃይማኖት በሰላም አብሮ መኖርን የሚደግፍ ነው” ሲሉ ዋና ጸሐፊው አስረድተዋል።አምባሳደር እንጂነር ማአሊም አያይዘውም የአለማቀፉ ማህበረሰብ በተለይም የእስልምና ሃይማኖት መሪዎች ይህን በሃይማኖት ሽፋን የሚንቀሳቀሰውን የአሸባሪ ቡድን ለመዋጋት በጋራ ሊቆሙ ይገባል ብለዋል።ኢትዮጵያውያን ህይወታቸውን አደጋ ላይ ከሚጥል ህገ-ወጥ የውጭ አገር ጉዞ እንዲታቀቡም ዋና ጸሐፊው ጥሪ አቅርበዋል።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/25382/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
d0fb7e45a9ee22014c055234510b284f
bf24d54e0e7f2f203d3d21e591724cc0
ኮማንድ ፖስቱ በሁከቱ የተሳተፉ አካላት አድኖ መያዝን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ  
ኮማንድ ፖስቱ በሁከትና ብጥብጥ ተሳትፈው ያልተያዙ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚያደርገው ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ ፡፡ኮማንድ ፖስቱ በሀገሪቱ ተከስቶ በነበረው ነውጥ ተሳታፊ የነበሩ እስካሁንም ያልተያዙ አካላትን አድኖ መያዝን አጠናክሮ መቀጠልን ጨምሮ ሌሎች አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የሶስት ወር አፈጸጸም ግምገማውን ትናንት አጠናቋል ።የኮማንድ ፖስቱ ሴክሬታሪያት እና የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ከአስቸኳይ አዋጁ በኋላ በመላ ሃገሪቱ አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን አረጋግጠው ፤ አሁንም አልፎ አልፎ የጸጥታ ችግሮች እንደሚስተዋሉ ጠቁመዋል ።ስለሆነም ኮማንድ ፖስቱ በሁከት እና ነውጥ ተሳትፈው ያልተያዙትን በቁጥጥር ስር ለማዋል አሁንም ተጨማሪ ስራ ያስፈልጋል የሚል ግምገማም ማስቀመጡን ነው ያስገነዘቡት ።ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋርም ከአፈጻጸም መመሪያው ባፈነገጠ መልኩ በፍተሻ እና ብርበራ ኬላዎች ከሚሰሩ ስራዎች ጋር ተያይዞ አቤቱታዎች እንደሚቀርቡ ነው የጠቆሙት ።በመሆኑም በየአካባቢው ያለውን አሰራር የመፈተሽ ስራ መሰራቱን ገልጸው፤ በህግ የሚጠየቁትን በህግ በስነ-ምግባር የሚጠየቁትን ደግሞ በስነ-ምግባር ተጠያቂ ከማድረግ አንጻር የተሰሩ ስራዎች ቀርበው ተገምግመዋልም ነው ያሉት ።እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ኮማንድ ፖስቱ በሀገሪቱ ተከስቶ በነበረው ሁከት እና ነውጥ ተሳታፊ የነበሩ እና እስካሁን በቁጥጥር ስር ያልዋሉ አካላትን አድኖ መያዝን የመጀመሪያው የትኩረት አቅጣጫው አድርጎም ነው ያስቀመጠው።የክልል ጸጥታ ሃይሎችን ይበልጥ ለማጠናከርም ከክልል መንግስታት ጋር በትብብር የተጀመረውን የማጽዳት፣ መልሶ የማደራጀት እና የማሰልጠን ተግባርን በመፈጸም ጠንካራ አቋም ያለው የጸጥታ ሃይል መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል ።ኮማንድ ፖስቱ በቀጣይ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ቁጥጥር እና የክልል ጸጥታ ሃይልን ይበልጥ የማጠናከር ስራ ላይ እንዲያተኩርም አመልክተዋል ፡፡ለመሰረተ ልማቶችና ፕሮጀክቶች የሚደረገውን ጥበቃ በማጠናከር ጥቃት እንዳይሰነዘርባቸው ማድረግ እና የሀገሪቱን ሰላም ዘላቂ ማድረግም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አረጋግጠዋል ።የህዝቡን ተሳትፎ ይበልጥ በማሳደግ ህዝቡ ራሱ የዘላቂ ሰላሙ መድህን እንዲሆን ማስቻልም ቀጣይ ተግባር ይሆናል ብለዋል ።ኮማንድ ፖስቱ ሀገሪቱን ወደ ቀደመ ሰላሟ የመመለስ ተግባሩን በአግባቡ መከወኑን ቀዳሚ ስኬት አድርገው አንስተዋል።በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በተለይም በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች፤ ይታይ የነበረው ሁከት እና ግርግር መክሰሙም አንዱ ማሳያ መሆኑን ነው የገለጹት ፡፡ነውጡን ሲመሩ የነበሩ ቡድኖችን መቆጣጠር መቻሉም ስኬታማ አፈጻጸም የታየበት መሆኑን አረጋግጠዋል ።በነውጡ ተሳታፊ የነበሩ ዜጎችን በቁጥጥር ስር በማዋል አስተምሮና አርሞ ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረግ ተግባር  ውጤታማ እንደነበር ጠቅሰዋል ።ሀገሪቱን ወደ ቀደመ ሰላሟ በመመለስ ሂደት ውስጥ ህዝቡ የራሱን ሚና እንዲጫወት የማድረጉ ወሳኝ እንደነበር  አቶ ሲራጅ  አስታውቀዋል  ።ኮማንድ ፖስቱ ግዙፍ የመሰረተ ልማት አውታሮችን፣ፋብሪካዎችንና አገናኝ አውራ ጎዳናዎች ጥቃት እንዳይፈጸምባቸው ያስቻለ ውጤታማ ስራ መስራቱንም አረጋግጠዋል።በሀገሪቱ ተከስቶ የነበረውን ሁከት እና ነውጥ በመደበኛ የጸጥታ ማስከበር ሂደት መቆጣጠር ባለመቻሉ ምክንያት የታወጀው አዋጅ አራተኛ ወሩን መያዙ ይታወቃል-(ኤፍ ቢ ሲ) ።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/28893/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c94908370299097ed87706f18e887409
f7524980b9a8bdfa7a83c99778d89da8
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሃርጌሳ በረራ ጀመረ
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 28/2005 (ዋኢማ) – የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሶማሊያ ላንድ ሃርጌሳ በ737 ቦይንግ አውሮፕላን አዲስ በተከፈተው ኢጋላ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ትላንት ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም በረራ አካሂዷል፡፡አየር መንገዱ ዓለም አቀፍ የበረራ መዳረሻዎቹን ቁጥር ለማሳደግ የሃርጌሳው በረራ አንዱ አጋዥ እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡የሶማሌ ላንድ የአቬየሽን ሚኒስትር ሞሃመድ ሃሺ አብዲ አዲስ የተጀመረው የበረራ መስመር በሁለቱ የምስራቅ አፍሪካ ሃገራ መካከል የንግድ ግነኙነታቸውን ያጠናክረዋል ብለዋል፡፡የኢጋላ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለአንድ ዓመት ያህል አስፈላጊ ዝግጅቶችና ማሻሻያዎች ሁሉ ከተደረጉለት በኋላ ከሣምንት በፊት ነው በይፋ የተከፈተው፡፡ በ1980ዎቹ የሶማሊያ የርስ በርስ ግጭት ጊዜ አየር መንገዱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ቢሆንም ላለፉት ዓመታት የማሻሻያ ሥራዎች ተሰርተውለታል፡፡ እንደ ኢሬቴድ ዘገባ 1960ዎቹ የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት ሙሃመድ ሃጂ ኢብራሂም ኢጋል ማስታወሻ እንዲሆንም አየር መንገዱ ኢጋል ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደተባለ ነው የተገለጸው፡፡
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/28094/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
2417b638deedd9360faa4f15142489d3
d0b4fe0c19ee12f6ae7fe31853b3af45
የተሻለ ነገን የመስራት ጥረት
‹‹ኢትዮጵያ በ2050›› በሚል ሀሳብ ትናንት በስካይ ላይት ሆቴል የተጀመረው ዓለምአቀፍ የውይይት መድረክ፤ በ32 ትውልደ ኢትዮጵያውያን ምሑራን (ፕሮፌሰሮችና ዶክተሮች) ተሰናድቶና በተግባር የተፈተሸ እውቀት ታግዞ 64 የጥናት ጽሁፎች የቀረቡበት ሲሆን በኢትዮጵያ የቀጣይ 30 ዓመታት ጉዞ ፈተናና መልካም እድሎች ላይ አተኩሮ እየተካሄደ ያለ ነው፡፡ በውይይት መድረኩ እንደተጠቆመው፤ ኢትዮጵያ ምንም እኳን በእድገት ጉዞ ላይ ብትሆንም በርካታ ችግሮች ያሉባት አገር ናት፡፡ በተለይም ለአንድ አገር ወሳኝ በሆኑ እንደ የትምህርት ጥራት፣ የሃይል አቅርቦት፣ የምግብ ዋስትና፣ በጤና ተደራሽነት እንዲሁም ትራንስፖርት በመሳሰሉ የእድገት መስኮች ወደኋላ ቀርታለች፡፡ ይሄን ችግር ከመፍታት አኳያ ደግሞ በርካታ ስራዎች መከናወን ያለባቸው ሲሆን፤ መድረኩ ሲዘጋጅም ቀደም ሲል በውጭ ያለው የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ከሚታወቅበት የፖለቲካ ተሳትፎ ባለፈ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገትና ልማት ውስጥ የበኩሉን እንዲወጣ ማስቻል ነው፡፡ በመሆኑም መድረኩ ከ30 ዓመት በኋላ ከሚኖራት የህዝብ ቁጥር አኳያ እነዚህን ችግሮች በምን መልኩ ፈትታ መጓዝ አለባት የሚለውን የሚያመላክትና የፖሊሲ ግብዓት የሚያቀርብ ይሆናል፡፡ ከአሜሪካ የመጡት ዶክተር ደብረወርቅ ዘውዴ፣ በመድረኩ ጽሑፍ ካቀረቡ ምሑራን አንዷ ናቸው፡፡ እርሳቸው እንደሚሉት፤ ምንም እንኳን ኢትዮጵያ በርካታ እድሎች ያሏትና በእድገት ጎዳናም ላይ ያለች ብትሆንም ዛሬም 78 በመቶ ያክል ህዝቧ የቀን ገቢው ከ2 ዶላር በታች ነው፡፡ ከ52 ሴቶች አንዷ በወሊድ ምክንያት ትሞታለች፡፡ 70 በመቶ ህዝቧ በጨለማ ውስጥ ይኖራል፤ የኢንተርኔት ተደራሽነቱም ቢሆን ከ15 እስከ 18 በመቶ ነው፤ የንጹህ ውሃ አቅርቦቱም ከ50 በመቶ ያነሰ ነው፤ የዘመናዊ መጸዳጃ ቤትም ከ15 በመቶ አልዘለለም፤ የጎልማሶች የትምህርት ምጣኔም 35 በመቶ ላይ ነው፤ በከተሞች ያለው የህዝብ እድገት ግን በሶስት እጥፍ እያደገ ይገኛል፡፡ ከዚህ ባለፈም የህዝብ ቁጥሯ እያደገ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እአአ በ2050፣ 200 ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል፡፡ እነዚህና ሌሎች የሚታዩ ችግሮች ከህዝብ ቁጥሩ እድገት ጋር ተዳምሮ ቀጣይ ስራን የሚጠይቁና ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊፈጸሙ የሚገባቸው ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ ለወጣቱ የሚመች ነገን ከመስራት ባለፈ ነገር የሚሰሩ ወጣቶችን መፍጠር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ጤናው ያልተጠበቀና ያልተማረ አምራች ሃይል ይዛ የትም መድረስ ስለማትችል፤ በወጣቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግና ወጣቱ ወደ አገር ግንባታ የሚገባበትን አቅም መፍጠር ይገባል፡፡ ለፈጣን እድገቷም በትምህርት እና ሴቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ ለእነዚህና ሌሎች ስራዎች እውን መሆን ደግሞ የመልካም አስተዳደር መስፈን ትልቅ ድርሻ እንዳለው ተገንዝቦ መስራት ይገባል:: ‹‹ኢትዮጵያውያን ጎበዝ ከተባልን ለምን ከዓለም ደሃ ህዝቦች መካከል ሆንን?›› የሚል ጥያቄን በማንሳት ሀሳባቸውን ያቀረቡት ሌላው የጽሑፍ አቅራቢ ኢንጂነር ታደሰ ሃይለስላሴ በበኩላቸው እንደሚሉት፤ ኢትዮጵያውያን ለእድገት ያላቸውን እድል ያክል ተግባብተውና ተጋግዘው መስራት ከቻሉ ከ30 ዓመት በኋላ የታሰበበት የብልጽግና ስፍራ የማይደርሱበት ምክንያት አይኖርም፡፡ ለዚህ ከሚያበቃቸው ዘርፍ አንዱ ግብርና ሲሆን፤ በተለይ ያላትን የውሃ ሃብት አጠቃቀም አዘምና በጤፍ ላይ አተኩራ መስራት አንዱ የብልጽግናዋ ጉዞ ማፋጠኛ መስክ መሆኑ እሙን ነው፡፡ ኢትዮጵያ ያሏት የልማት እድሎችና የመልሚያ መንገዶች ከቦታ ቦታ የተለያዩ መሆኑን የሚናገሩት ኢንጂነር ታደሰ፤ በምዕራብና ምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን የውሃ ሃብት ለአብነት ያነሳሉ፡፡ በዚህም ውሃን ከምዕራቡ ክፍል ወደ ምስራቁ መፍሰስ እንዲችል ማድረግ አንዱ መንገድ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ለምሳሌ፣ ከእንጦጦ ጀርባ ካሉ አካባቢዎች ወደ ጀማ ወንዝ ገብተው ከአባይ ወንዝ የሚቀላቀሉ 13 ጅረቶች አሉ፡፡ እነዚህን ወደ አንድ ሰብስቦ በአዲስ አበባ በኩል ወደ ምስራቁ እንዲፈሱ ማድረግ ቢቻል እስከ 2 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃን ማመንጨትና በውሃውም እስከ 150 ሺህ ሄክታር መሬት ማልማት ይቻላል፡፡ ለዚህ ደግሞ መንግስት፣ ባለሀብቱ፣ ባለሙያዎችና ሌሎችም የልማት አጋሮች ተገቢውን ትኩረትና ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሌላው ጥናት አቅራቢ ፕሮፌሰር አስፋው በየነ እንደሚሉት፤ የአየር ንብረት ለውጥ አሁን ላይ ዓለምን ለበርካታ ውስብስብ ችግሮች እየዳረገ ያለ ጉዳይ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ትልቅ ሚና አለው፡፡ የካርቦን ዳይኦሳይድ ምንጭ ደግሞ በአመዛኙ ከመሬት ተቆፍረው የሚወጡ ነገሮች ናቸው፡፡ እነዚህ ተቆፍረው የሚወጡ ማዕድናትና ሌሎችም ለከባቢ አየር መበከል የጎላ ሚና አላቸው፡፡ አሁን ላይ የከባቢ አየር ሙቀት መጨመርም የዚህ አንድ ማሳያ ሲሆን፤ ኢትዮጵያም በዚህ መልኩ ለሚፈጠረው አየር ንብረት ለውጥ ተጠቂ አገራት መካከል አንዷ ናት፡፡ ኢትዮጵያ በማይገመት የዝናብ ሁኔታ ውስጥ ሆና በዝናብ ላይ የተንጠለጠለ ግብርናን ይዛ ከረሃብና ድህነት መውጣት አትችልም፡፡ በመሆኑም የግብርና ስልቷን መቀየር፤ በተለይም የመስኖ ልማት ስራ ላይ ማተኮር ይኖርባታል፡፡ ለዚህ ደግሞ ከወረቀት የዘለለ የሚተገበር ፖሊሲ ቀርጻ መስራት ይጠበቅባታል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት ዶክተር የውሃ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው እንዳሉት፤ መሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት ለኢትዮጵያ ኦኮኖሚ ወሳኝ ጉዳዮች ናቸው፡፡ ለእነዚህ ውጤታማነት ደግሞ ውሃ ወሳኝ ድርሻ አለው፡፡ ይሁን እንጂ የውሃ ሀብታችን፣ አንደኛ በአመዛኙ ድንበር ተሻጋሪ በመሆኑ፤ ሁለተኛም በአካባቢ ጥበቃ ችግር ምክንያት እየተመናመነ በመሆኑ በአግባቡ ጥቅም ላይ እየዋለ አይደለም፡፡ ለምሳሌ፣ እንደ ህዳሴ ግድብ አይነቱን በድንበር ተሸጋሪ ወንዞች ላይ የሚከናወነውን የልማት ስራ ማየት ቢቻል ከሌሎች አገራት ጋር ተባብሮና ተግባብቶ መስራትን ይጠይቃል:: ለዚህም ኢትዮጵያ የድርሻዋን እየተወጣች ነው፡፡ በተመሳሳይ በደን መጨፍጨፍና በመሬት መሸርሸር ምክንያት የውሃ ሀብት እየተጎዳ ይገኛል፡፡ ይሄንንም ለመከላከል ሰፊ የአካባቢ ጥበቃ ስራ እያከናወነች ነው፡፡ እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ኢትዮጵያ ካላት እምቅ ሀብትና የመልማት አቅም አኳያ አሁን ላይ ያለው ነገር በቂ የማይባል፤ ይልቁንም ብዙ መስራትን የሚጠይቅ ነው:: በዚህም የውሃ ሀብቱን ቀጣይነት ልማትና አስተዳደር ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፤ ባለፈው ክረምት የተከናወነው የአራት ቢሊዮን ችግኝ መርሃ ግብርም የዚሁ አንድ አካል ነው፡፡ ይህ ስራም ከሌሎች አጋዥ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ጋር ተመጋግቦ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ይህ ሲሆን የውሃ ሀብቱን በማሳደግ የልማቱን ጉዞ ማፋጠን ይቻላል፡፡ በዚህም የመስኖ ልማት፣ የሃይል ማምረት፣ የንጹህ መጠጥ ውሃና ሌሎችንም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ልማቶችን ማፋጠን የሚቻልበት እድል ይፈጠራል፡፡ የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ አሁን ላይ በአስገራሚ ለውጥ ላይ ናት፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እርምጃዎችም የዚሁ ማሳያዎች ሲሆኑ፤ የሰላም ኖቤል ሽልማቱ፣ የአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው እና ሌሎችም የዚሁ ጉዞ ማሳያዎች ናቸው፡፡ ከስራ እድል ፈጠራ፣ ከኢንቨስትመንት ማስፋፊያና የውጭ ባለሀብቶችን ለማበረታታት የሚደረገው ጥረትም የስራው አጋዥ ነው:: አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ለውጥና የመደመር እሳቤ ጉዞ የበርካታ አገራትን ወዳጅነትና የኢንቨስትመንት ተፈላጊነት እያሳደገላት ይገኛል፡፡ አገር በቀል የሆነው የመደመር እሳቤም የአገሪቱን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች በራሷ እውቀት ለመፍታት እድል የሚሰጣት ነው፡፡ መንግስትም በአገሪቱ ሁለንተናዊ እድገትና ልማት ብሎም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ዘርፉ ላይ የዳያስፖራው ተሳትፎ እንዲያድግ በፖሊሲና በተግባር እቅድ ይደግፋል ብለዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2012 ወንድወሰን ሽመልስ
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=24414
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f1009bb980e176052966529fba4d4339
cffc9478f096d49e4da1aebd5e7a8956
በኢትዮጵያ ለ650 የህግ ታራሚዎች ይቅርታና ምህረት ተደረ
በኢትዮጵያ ለ650 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታና ምህረት ተደርጎ በመፈታት ላይ መሆናቸው ተገለጠ፡፡የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ የይቅርታ ቦርድ በሐምሌ 28/2010 ዓ.ም ባሳለፈው የውሳኔ ሀሳብ መሰረት ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ ታራሚዎቹ እንዲፈቱ እየተደረገ መሆኑ ታውቋል።በሀገር ውስጥ ዘገባዎች መሰረት ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች ድሬደዋ፣ ከቃሊቲ፣ ዝዋይ እና ቂሊንጦ ማራሚያ ቤት የሚገኙ ናቸው።ታራሚዎቹ በይቅርታ አዋጁ መስፈርት መሰረት በልዩ ሁኔታ ማለትም በዕድሜ መግፋት፣ በከባድ ጤና ችግርና የተፈረደባቸውን ፍርድ አንድ ሦስተኛ የጨረሱ እንዲሁም የገንዘብ ቅጣታቸውን የከፈሉ እንደሚገኙባቸው ዘገባው አመልክቷል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/ethiopia-prisoners-released-8-23-2018/4541183.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7304147235aa01e3add96cd891d39c31
eabc9e7ddfd70413a71d336acc67b51a
ሕብረተሰቡ ፖሊስ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ ሊተባበር ይገባል – ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሕብረተሰቡ ፖሊስ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ ትብብር እንዲያደርግ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው ጠየቁ።የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ቢሮ ሜክሲኮ አደባባይ ገነት ሆቴል አካባቢ በሚገኘው የቀድሞው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሥራ ጀምሯል።የቀድሞው የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ከተዘጋ በኋላ ካዛንቺስ በሚገኝ ህንጻ ላይ ተጠርጣሪዎችን ሲመረምር እንደነበር ታውቋል።ኮሚሽኑ ሕንፃውን ላለፉት ሶስት ወራት እድሳት ሲያደርግ ቆይቷል።ጥራታቸውና ደህንነታቸውን የጠበቁ የተጠርጣሪዎች የቃል መቀበያና ማቆያ እንዲሁም የጠበቆችና የባለጉዳዮች መቀበያ ክፍሎችንም አዘጋጅቷል።ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኮሚሽኑ ሕንጻውን ከተረከበ በኋላ ያከናወነው እድሳት የቀለምና የቁሳቁስ ብቻ አልነበረም።ይልቁንስ ተጠርጣሪዎች ያለማንም አስገዳጅነት በራሳቸው ፍላጎት ከፍርሃት ነጻ ሆነው የሚመረመሩበት የአስተሳሰብ እድሳት ጭምር ነው ብለዋል።በመሆኑም ኅብረተሰቡ ፖሊስ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የሚደርገው የወንጀል ምርመራ የዜጎችን ክብር በጠበቁ መልኩ መሆኑን በመገንዘብ እንዲተባበረው ጠይቀዋል።የኮሚሽኑ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግሥቴ በበኩላቸው የምርመራ ሥራዎች በዘመናዊ መንገድ የሚያከናውንበት እድሳት መደረጉን ገልጸዋል።ቢሮው ሰዎች ሲያዩት የሚፈሩት ሳይሆን፤ በነጻነት ሃሳባቸውን የሚገልጹበት አደረጃጀት እንዲኖረው ተደርጓልም ብለዋል።ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም፥ በቢሮው የተጠረጠረ ማንኛውም ግለሰብ ከቤተሰቦቹም ሆነ ከጠበቆቹ ጋር መገናኘት ይችላል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%88%95%e1%89%a5%e1%88%a8%e1%89%b0%e1%88%b0%e1%89%a1-%e1%8d%96%e1%88%8a%e1%88%b5-%e1%8b%a8%e1%88%95%e1%8c%8d-%e1%8b%a8%e1%89%a0%e1%88%8b%e1%8b%ad%e1%8a%90%e1%89%b5%e1%8a%95-%e1%88%88%e1%88%9b/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e70f51eaa88f5ac33f5793c7d2774ab1
bfd559a35a5a37557c49aeb55f2279ac
የሁሉም ቤተ ዕምነቶች ተከታዮች ለአገሪቱ ሰላምና መቻቻል መጠናከር እንዲሠሩ ጥሪ ቀረበ
የኢትዮጵያ የሃይማኖቶች ተቋማት ጉባኤ በዛሬው ዕለት አምስተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ባካሄደው ስብሰባ ላይ የጉባኤው ጠቅላላ ጸሃፊ መጋቢ ዘሪሁን ደጉ እንደገለጹት ሰላምና መቻቻል  ለአገሪቱ ሰላማዊ የምርጫ ሂደትና ዘላቂ  ዕድገት ያለው  ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ የሁሉም ቤተ ዕምነት ተከታዮች ሰላምና መቻቻልን ይበልጥ እንዲጎለብት የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል ።በሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ስብሰባ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እንደተናገሩት ጉባኤው የሰላም ጥሪ መድረክ በማዘጋጀቱ ምስጋናቸውን አቅርበው በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደው ምርጫ በተሰካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ቦርዱ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል ።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ማቲያስ በበኩላቸው በአገሪቱ ሰላም መጠበቅ ለዜጎች ህልውና ወሳኝ ከመሆኑም በላይ ተጨማሪ ልማትን ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑንና ህዝቡ በሰላማዊ ምርጫ ሂደት የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ አባታዊ መልዕክታቸውን አሰተላልፈዋል ።የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሐጂ መሐመድ አሚን በበኩላቸው እንደገለጹት ምርጫው በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚደረግ ውድድር ቢሆንም ጉዳዩ የህዝብ በመሆኑ የትኛውም ውጤት ይገኝ ፓርቲዎች በጸጋ መቀበልና በአገራዊ ጉዳይ ላይ መቻቻልና መከባበርን ማሳየት አለባቸው ብለዋል።የኢትዮጵያውያ ካቶሎሊካውያን ጳጳሳት ጉባኤ ካርዲናልብርሃነ እየሱስ ምርጫዎች የህዝብ ውሳኔ  ነጸብራቆች በመሆናቸው እያንዳንዱ ዜጋ ከምርጫ በፊት፤ በምርጫ ወቅትናከምርጫ በኋላ  ለአገሩ  የጋራ  ጥቅም ሲባል ንቁ ተሳትፎ ማድረግ አንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል ።የኢትዮጵያውያን ወንጌላዊት አንድነት ህብረት ዋና ጸሃፊ ቄስ አለሙ ሺጣ በበኩላቸው ህዝቡ ይመራኛል የሚለውን  ፓርቲ በመመምረጥ የዜግነት ኃላፊነቱን በመወጣት  ምርጫው ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ለዕምነት ተካታዮቻቸው በሙሉ ጥሪ አስተላልፈዋል ።የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያንና የኢትዮጵያ ዩኒኤን ሚሽን ፕሬዚዳንት ፓስተር ዶክተር ዓለሙ ኃይሌ በአገሪቱ ምርጫ ሁሉም የራሱን አስተዋጽኦ በማድረግ   ለየአኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን እንደሚረዳ ጥሪ አስተላልፈዋል ።የፖለቲካ አመለካካት ልዩነትን በማክበር  የሚደረግ ምርጫ በሕዝቦች መካከል  የፍቅርና አንድነትን መንፈስን የሚያጎለበት በመሆኑ ፍጹም  ዴሞክራሲያዊ  ሥርዓት በማስፈን  ምርጫው ሂደት እንዲካሄድ የኢትዮጵያ ቃለ ህይወት ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ተከተል ዮሃንስ ጥሪ አስተላልፈዋል ።በመጨረሻም ጉባኤው በገሪቱ ከጥንት ጀምሮ በተለያዩ ሃይማኖቶች መካካል የዳበረውን የመከባበር  እሴት በፖለቲካው እንዲደገም  የተለያዩ ቤተ ዕምነት ተከታዮች በጸሎት እንዱተጉ ጉባኤው ጥሪ አቅርቧል ። 
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/25389/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
aa80469b1aeaeecbf46038af5e5d2477
982986101bc0dcb4fb98ac2c435347af
ኦሊምፒክ ኮሚቴ አትሌቶችን እደግፋለሁ አለ
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ከውድድር ውጪ ለሆኑ ብሔራዊ አትሌቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ተጠሪነቱ ምንም እንኳ ለሁሉም ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ቢሆንም፣ ብሔራዊ አትሌቶችን በሒደት ከገንዘብ ድጎማ ጀምሮ የተለያዩ ድጋፎችን ለማድረግ እየሠራ መሆኑ ፕሬዚዳንቱ ዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ አስታውቀዋል፡፡ ከድጋፉ ባሻገር የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (አይኦሲ) የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከመከሰቱ በፊት ለአገሮች በሰጠው ነፃ የትምህርት ዕድል ኮታ መሠረት ኤሊት አትሌቶች ዕድሉን እንዲጠቀሙ ለማድረግ ሥራዎችን እየሠራ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ ብሔራዊ ተቋማት ችግሩ በአትሌቶች ላይ ሥነ ልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና እንዳያሳድር የሚችሉትን እያደረጉ ይገኛሉ። ቀደም ሲል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት አትሌቶችንና መሰል ሙያተኞችን መደጎሙ አይዘነጋም፡፡ አዲስ ዘመን ሚያዝያ 27/2012
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=31712
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
fa7d87d701647705752abdd2208ed562
3a21832e3d2edb5addb15ceea82e9dcf
ከአምልኮ ቦታ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ 'ግጭት' 7 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተነገረ
በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ መግለጫ የሰጡ ሲሆን፤ እስካሁን ከግጭቱ ጋር በተያያዘ 7 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ተናግረዋል። ምክትል ከንቲባው ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉት 7 ሰዎች መካከል አመራሮች ይገኙበታል ቢሉም አመራሮቹ የኃላፊነት ደረጃ አልጠቀሱም። ምክትል ከንቲባው ከሰዓታት በፊትም በፌስቡክ ገጻቸው ላይ በግጭቱ የሁለት ወጣቶች ህይወት ማለፉ እንዳሳዘናቸው ገልጸው "በየትኛውም ወገን ያሉ የጥፋቱ አካላትን በሕግ እንዲጠየቁ እናደርጋለን" ብለው ነበር። የሚፈልጉት ይዘት የለም የ Facebook ይዘት መጨረሻ, 1 ምክትል ከንቲባው ከይዞታ ይገባኛል ጥያቄዎች ጋር በተያያዘ አስተዳደራቸው ጥያቄዎችን ሲመልስ መቆየቱን አመልክተው፤ "በመንግሥት እና በሐይማኖት ተቋማት ውስጥ በሚገኙ ጥቂት አጥፊዎች ምክንያት በከተማችን ይሆናል ያላልነው፤ እንዳይሆንም የለፋንበት ድርጊት ተፈጽሟል" በማለት ሃዘናቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ብፅዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አመሻሽ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ቤተክርስቲያኗ ትናንት ምሽት በተፈጠረ አለመግባባት የሁለት ወጣቶች ህይወት ማለፉ እንዳሳዘናት ገልጸዋል። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጉዳዮችን በውይይትና በሰከነ መንፈስ መፍታት እየተቻለ የተፈጠረው ችግር ተገቢ ያልሆነ እና መፈጠር የሌለበት ነው ብለዋል። የወንጀል ምርመራወእን ሂደት ዝርዝር ሪፖርት ለህዝብ ይፋ እንዲሆንም ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን የአዲስ አበባ ሐገረ ስብከት የካህናት አስተዳዳር ኃላፊ የሆኑት መላዕከ ሕይወት አባ ወልደየሱስ ሰይፉ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት በግጭቱ ሁለት ወጣቶች በጥይት ሲገደሉ ሌሎች ደግሞ ቆስለው ሆስፒታል ገብተዋል። ግጭቱ የተቀሰቀሰው በአካባቢው ባለ አንድ የታጠረ ቦታ ምክንያት መሆኑን ለቢቢሲ የገለጹት ነዋሪዎች ፖሊስ ለምን እርምጃውን በወድቅት ሌሊት መውሰድ እንደፈለገ እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው ተናግረዋል። • "የደባ ፖለቲካውን ማስቆም ፈተና ሆኗል፤ ግን ኢትዮጵያን የምናስቀጥል መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ" • "የተማሪዎቹ ዕገታ እንደ አገር ከገጠሙን ችግሮች አንዱ ነው" ም/ጠ/ሚ ደመቀ መላዕከ ሕይወት አባ ወልደየሱስ ስለክስተቱ ለቢቢሲ እንደተናገሩት "ለመንፈሳዊ ክብረ በዐል ዝግጅት እየተደረገ፣ ኅብረተሰቡ ፀሎት እያደረገ እያለ ነው በአሳቻ ሰዓት ላይ ከሌሊቱ ስድስት ተኩል ጀምሮ ፖሊስ እርምጃ መውሰድ የጀመረው።" የቦታውን ባለቤትነት በተመለከተ ከአስር ዓመት በፊት ጥያቄ ቀርቦበት በጊዜው በመንግሥት ባለስልጣናት መቀያየር ምክንያት ምላሽ ሳያገኝ የቆዬ ሒደት እንዳለ ጠቅሰው "የአዲስ አበባ ሐገረ ስብከት ይፋዊ ደብዳቤ ለወረዳው ፅፎ እየተከታተለ ነበር" ብለዋል። መላዕከ ሕይወት አባ ወልደየሱስ ሰይፉ አክለውም በክስተቱ የሞቱ ወጣቶችን ቤተሰቦችን በማግኘት ማፅናናታቸውንና ጉዳት የደረሰባቸውንም ለማግኘት እየሞከሩ መሆኑን ተናግረዋል። ቢቢሲ በትክክል የተፈጠረውን እንዲሁም የደረሰውን ጉዳት ለማጣራት ለፌደራል ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ቢደውልም፤ ጉዳዩን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስን ማነጋገር እንዳለበት ተነግሮታል። የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር ፋሲካ ለተደጋጋሚ የስልክ ጥሪዎች እና የፅሁፍ መልዕክቶች ምላሽ አልሰጡም። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ስልክም እንዲሁ ሳይመለስ ቀርቷል። ሌሊት ምንድን ነው የተከሰተው? ማክሰኞ ሌሊት ተኩስን ያስተናገደው ሃያ ሁለት በተለምዶ ቀበሌ 24 አካባቢ ረቡዕ ማለዳ የፀጥታ ኃይሎች ተበራክተውበት ተስተውሏል።...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
efa500fea3013dbd0c44585e3f141606
bb804f939d99e3241b80cf0b137eb99d
በዓመታት ውስጥ ከመቶ ቢሊዮን ብር በላይ ጭማሪ ያሳየው የኢትዮጵያ በጀት
ከዚህም ውስጥ ለመደበኛ ወጪዎች 109 ቢሊዮን፣ ለካፒታል ወጪዎች 130 ቢሊዮን፣ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ 140 ቢሊዮን እንዲሁም ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ መመደደቡን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል። ይህ ለቀጣይ ዓመት የተያዘው ሃገራዊ በጀት ላለንበት 2011 ዓ.ም ከተያዘው ጋር ሲነጻጸር በ11.5 በመቶ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፤ ከባለፈው 2010 ዓ.ም ጋር ደግሞ በ20.6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። •‹‹እነ ቴሌን ለግል ባለሀብት?›› ታሪካዊ ስህተት ወይንስ መልካም አጋጣሚ ? •ኢትዮጵያ ከውጭ ምንዛሬ እጥረት አዙሪት እንዴት ትውጣ? ይህም በመጠናቀቅ ላይ ባለው ከ2011 ዓ.ም በጀት ጋር ሲወዳደር ከአርባ ቢሊዮን ብር በላይ ጭማሪ አሳይቷል። በዚህ በጀት ዓመት 346 ቢሊዮን 915 ሚሊዮን 451 ሺ 948 ተመድቦ የነበረ መሆኑ የሚታወስ ነው። ለመደበኛ ወጪ 91 ቢሊዮን 67 ሚሊዮን 160 ሺ 588 ብር እንዲሁም ለካፒታል ወጪ 113 ቢሊዮን 635 ሚሊዮን 559 ሺ 980 ተመድቦ ነበር። ይህ በጀት በ2010 ዓ.ም ከፀደቀው አንፃር የ3.6 በመቶ ጭማሪ እንደነበረውም ተገልጿል። በ2010 የነበረው በጀት 320.8 ቢሊዮን ብር ሲሆን፤ ከ60 በመቶ የሚበልጠው ለትምህርት፣ ለግብርናና ለመሰረተ ልማትና ለጤና ማስፋፊያ እንዲሆን ተብሎ የተበጀተ ገንዘብ ነበር። •የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት ኢኮኖሚያዊ ትርፍ? ከ300 ቢሊዮን ብር በታች የነበረው የኢትዮጵያ ዓመታዊ በጀት በ2009 ዓ.ም ላይ 274.3 ቢሊዮን በጀት ተመድቦ ነበር። የፌደራል የመንግሥት በጀት በአራት ዓመታት ውስጥም ከመቶ ቢሊዮን ብር በላይ ጭማሪ አሳይቷል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት የቀጣይ ዓመት የሃገሪቱ በጀትን በተመለከተ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪ ለሆነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ መጽደቅ ይኖርበታል። ከዚህ በፊት ከነበረው ልምድ በመነሳት የቀረበው በጀት ያለችግር እንደሚጸድቅ ሲሆን ምክር ቤቱም የዓመቱን የሥራ ጊዜውን ከማጠናቀቁ በፊት የጨረሻው ውሳኔ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
eef9c588d7f5e8c34ac0bfe40f275a5a
f5765ced9db722df17974c0c1192fa9c
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዜጋ ተኮር እና ጎረቤት ተኮር ዲፕሎማሲ ላይ ትኩረት ሰጥቼ እየሰራሁ ነው አለ።
"የኢትዮጵያ መንግሥት የሚከተለው ዲፕሎማሲ ቀለም አልባ ነው" የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር\nሚኒስትሩ ዛሬ ሐሙስ ማለዳ በሰጠው መደበኛ ጋዜጣዊ መግለጫው የኢፌድሪ መንግስት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት ላይ የማይተካ ሚና አላት ብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ከኤርትራው አቻቸው ኦስማን ሳለህ ወደሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ ያደረጉት ከጥቂት ቀናት ጉብኝት የጎረቤት ተኮር ዲፕሎማሲ አንድ ማሳያ ነው ያሉት የሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም ናቸው። •ሃምሳ በመቶ የሚኒስትሮች ሹመት ለሴቶች •ከጄኔራሎቹ ሹመት ጀርባ? •የአዲስ አበባ ወጣቶች በሳምንቱ መጨረሻ እንደሚለቀቁ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ ሚኒስትር ወርቅነህ በሶማሊያ ጉብኝታቸው ወቅት የአፍሪቃ ቀንድ ሰላም እና ደህንነት እውን እንዲሆን እንዲሁም ለቀጠናው ምጣኔ ኃብታዊ ትስስር በጋራ ለመስራት ከኤርትራ እና ሶማሊያ አቻዎቻቸው ጋር መወያየታቸውን ይህንንም የሚያስረግጥ የጋራ መግለጫ መስጣታቸውን አቶ መለስ አክለው ተናግረዋል። በሶስቱ አገራት መካከል በኤርትራ ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። "ጎረቤትን የሚያስቀድም ዲፕሎማሲ፣ የጎረቤቶቻችን እጣ ፈንታ ከእኛ ጋር የተሳሰረ ነው በሚል ፅኑ እምነት ላይ የተመሠረተ ነው" ብለዋል አቶ መለስ። የኢትዮጵያ መንግስት የሚከተለውን ዲፕሎማሲ "ቀለም አልባ ነው" ሲሉም ገልፀውታል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በቅርቡ በፈረንሳይ እና በጀርመን በሚያደርጓቸው ጉብኝቶች በአፍሪካ ቀንድ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ቃል አቀባዩ ጨምረው ተናግረዋል። ጥቅምት 21 ቀን"አንድ ሆነን እንነሳ፤ ወደፊቱን እንገንባ" በሚል መሪ ቃል በአውሮፓ የኢትዮጵያዊያን ቀን ይከበራል። በዕለቱም በአውሮፓ ያሉ ኢትዮጵያዊያን በጀርመኗ ፍራንክፈርት ይሰበሰባሉ ተብሏል። እንደአቶ መለስ ገለፃ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ድኤታ ወይዘሮ ብርቱካን አያኖ የሚመራ እና በርካታ ታዋቂ ግለሰቦች የተካተቱበት ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ ስራ ጀምሯል። "ሦስት ሚሊዮን የሚጠጉ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የማይሳተፉበት የአገር ግንባታ ሒደት ስኬታማ አይሆንም" ሲሉ አቶ መለስ የዕለቱን አስፈላጊነት አብራርተዋል። "በቀድሞ በሬ በማረስ ለውጥ ማምጣት አይቻልም፤ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል። እነርሱም የአገራቸው ጉዳይ ያገባቸዋል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያዊያኑ ጋር ተገናኝተው፤ እየተካሄድ ስላለው ለውጥ ያስረዳሉ፤ ኢትዮጵያዊያኑ ሊኖራቸው የሚችለውን አስተዋፅዖ ይገልፃሉ፤ እንዲሁም የኢትዮጵያዊያኑን ራዕይ እና ፍላጎት ያዳምጣሉ እንደቃል አቀባዩ ገለፃ። አውሮፓ ውስጥ በሚገኙ 13 ሚሲዮኖች እና የቆንስላ ፅህፈት ቤቶች ዝግጅቶች እየተከናወኑ ሲሆን ከ20 ሺህ እስከ 25 ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን እና የኢትዮጵያ ዝርያ ያላቸው ዜጎች ይገኛሉ ተብሎም ይጠበቃል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የመዋቅር ማሻሻያ እያደረገ ነው፤ ይህም በሚሲዮኖች እንዲሁም በዋናው መስሪያ ቤት ውስጥ ይከናወናል ብለዋል አቶ መለስ። "ይሄንን ተቋም የሃያ አንደኛውን ክፍለ ዘመን የሚመጥን ማድረግ ያስፈጋል፤ እንደዚያ ዓይነት ተቋም ለመፍጠር የሚያስችል የማሻሻያ ሥራ እየተካሄደ ነው።"
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
b9935b06f8f6bb6f1c3803b15fb880a1
856657fbe787f395c36693d1f33c347d
መከላከያ 1-3 ምስር አል ማቃሳ – ከጨዋታ በኋላ የተሰጡ አስተያየቶች 
 በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ቅድመ ማጣርያ የግብፁ ክለብ ምስር አል ማቃሳ መከላከያን 3-1 አሸንፏል፡፡ ከጨዋታው በኃላ የመከላከያው አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ እና የማቃሳው አሰልጣኝ ኤሃብ ጋላል ለጋዜጠኞች አሰተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ “ደካማ ጎናቸው አልታየኝም” አሰልጣኝ ገ/መድህን ኃይሌ ስለጨዋታው“ጨዋታው ጥሩ አልነበረም፡፡ ተጋጣሚያችን በጣም ጠንካራ ነበር፡፡ ጥንካሬያቸውን ብናውቅም ጨዋታው እንደተጀመረ ግብ ያስቆጥሩብናል ብለን አልጠበቅንም ነበር፡፡ የምንፈጥራቸው ስህተቶች ናቸው ግብ እንዲቆጠር የሚዳርጉት፡፡ ከዕረፍት መልስ ጥሩ ለመንቀሳቀስ ሞክረናል፡፡ ነገር ግን ውጤቱን ለመቀየር አስቸጋሪ ነበር፡፡ ክፍተት ስለታየበት የተከላካይ መስመር” አሁንም ባሉን ተጫዋቾች ነው የምንጠቀመው፡፡ ሌላ ምንም አማረጭ የለንም፡፡ በአጠቃላይ በቡድን ደረጃ ከተጋጣሚያችን ጋር ሰፊ ልዩነት አለን፡፡ ” ስለተጋጣሚያቸው“ደካማ ጎናቸው አልታየኝም፡፡ እውነት ለመናገር አል ማቃሳ በጣም ጥሩ ቡድን ነው፡፡ ይህን ከዚህ በፊትም ያየሁት ነገር ነው፡፡  በጋራ በቁጥር በዝተው ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፡፡ በሊጋቸውም ላይ ጥሩ ሲጫወቱ አይቻለው፡፡ ከኛ ጋር ሲጫወቱ የነሱን ድክመት ማወቅ አልቻልንም፡፡ ” ስለመልስ ጨዋታው” በሜዳችን 3-1 ተሸንፈናል፡፡ ከሜዳችን ውጪ ቢያንስ 3-1 ማሸነፍ መቻል አለብን፡፡ ይህንን ማድረግ ከባድ ነው ፣ ቀላል ነው አልልም፡፡ የተወሰኑ ነገሮችን ለማስተካከል እንጥራለን፡፡ በመስመር በኩል የነበረብንን ድክመት ለማሻሻልም እንሞክራለን፡፡ ዕድል ያልጠሰጣቸውን ተጫዋቾች ለመሞከር እንጥራለን፡፡ ”” ጨዋታው አልተጠናቀቀም” ኤልሃብ ጋልአልስለጨዋታው“ለኔ ጥሩ ውጤት ነው፡፡ ለኛ ይህ የመጀመሪያ የአህጉራዊ ውድድር ጨዋታ ነበር፡፡ ጥሩ ቡድን አሸንፈን መልካም ጅማሮ አድርገናል፡፡ በሁለተኛው አጋማሽ ላይ ጥሩ መንቀሳቀስ አልቻልንም ነበር፡፡ 2-0 መምራት ከጀመርን ጀምሮም ትንሽ የመዘናጋት ነገር ይታይብን ነበር፡፡” ዓየር ፀባዩን ለመልመድ አስቸግሮናል፡፡ በተጨማሪም ስምንት እና ዘጠኝ የሚሆኑት ተጫዋቾቻችን ለዚህ ውድድር አዲስ ናቸው፡፡  ተጋጣሚያችንም በሁለተኛው አጋማሽ ተጭኖ መጫወቱ ለኛ ከባድ ነበር፡፡ ” ስለመልስ ጨዋታ” ጨዋታውን ማሸነፋችን ሊጠቅመን ይችላል፡፡ ነገር ግን ገና አልተጠናቀቀም፡፡ ለካይሮ ጨዋታ ራሳችንን ማዘጋጀት አለብን፡፡ ” ስለተጋጣሚያቸው” መከላከያ ጥሩ ቡድን ነው፡፡ ጥሩ ኳስ ይጫወታሉ፡፡ በብዛት ረጃጅም ኳሶችን መጫወትን እንደሚመርጡ ስላወቅን ተዘጋጅተን ነበር፡፡ ቢሆንም ሶስት የጠሩ የግብ ማግባት ዕድሎችን አግኝተው ነበር፡፡ ሁለት ተጫዋቾች (ሙሉዓለም እና ፍሬው)ጥሩ ይንቀሳቀሳሉ፡፡ ቡድኑ 3-0 እየተመራም ተስፋ አልቆረጠም፡፡ ይህ የመከላከያ ጠንካራ ጎን ነው፡፡”
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/5451
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
717e6db74619166e6b47227d00b93ddb
6b9b87cd651807d48a7725cacb805575
በህንድ ደልሂ ግዛት የተደፈረችው ህፃን በአስጊ የጤንነት ሁኔታ ትገኛለች
ጥቃቱን ፈፅሟል የተባለውና በቁጥጥር ስር የዋለው የ40 ዓመቱ ተጠርጣሪ የፀጥታ አስከባሪ ሲሆን ህፃናት በሚኖሩበት ህንፃ ተቀጥሮ ይሰራ ነበር። •የተነጠቀ ልጅነት • ሀና እና ጓደኞቿ የሰሩት የእናቶች ምጥ መቆጣጠሪያ •የ7 ዓመቷ ህጻን ግድያ፡ ''ከልክ ያለፈ ቅጣት የልጄን ህይወት አሳጣኝ'' በወቅቱ ፖሊስ ራሷን ስታ ያገኛት ሲሆን በአፋጣኝ ወደ ሆስፒታል ተወስዳ አስፈላጊው ህክምና እየተደረገላት ይገኛል። በአገር አቀፍ ደረጃ ቁጣን በቀሰቀሰውና ከዚህ ቀደም በአውቶብስ ውስጥ በቡድን የተደፈረችዋን ተማሪ ስድስተኛ ዓመት ዝክር ወቅት ድርጊቱ እንደተፈፀመ በደልሂ የሴቶች ኮሚሽነር ስዋቲ ማሊዋል ገልፀዋል። እስካሁን ድረስ ህፃኗ ከጉዳቷ ልታገግም መቻል አለመቻሏን በተመለከተ ግልፅ የሆነ መረጃ ባይኖርም ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት ነው ሲሉ የአገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ተጠርጣሪው ጥቃቱን ሲፈፅም በቀን ስራ የሚተዳደሩት የህፃኗ ቤተሰቦች ለስራ ወጥተው ነበር፤ ከዚያም ህፃኗን ከረሜላ በመስጠት ከቤት ይዟት እንደወጣ ታውቋል። ተጠርጣሪው ጥፋተኛ ሆኖ ከተረጋገጠ እስከሞት የሚደርስ ቅጣት ሊያስቀጣው እንደሚችል ፖሊስ አስታውቋል። በህንድ በዚህ ዓመት ብቻ በህፃናት ላይ በተከታታይ የደረሱ ጥቃቶችን ተከትሎ አዲስ ቁጣ ቀስቅሷል፤ ባለፈው ሚያዚያ ወር አንዲት የስምንት ዓመት ህፃን በቡድን የመድፈር ጥቃት ተፈፅሞባታል፤ ባለፈው ሰኔ ወርም እንዲሁ የ7 ዓመት ህፃን ልጂ መደፈሯን ተከትሎ በማዕከላዊ ህንድ ግዛት ማዲህያ ፓራደሽ ተቃውሞ ተነስቶ እንደነበር ይታወሳል። በህንድ የሚፈፀም ጥቃት የህንድ መንግስትና የተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) መረጃ መሰረት
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
000fcbeb2b2f16f8566b026007471096
332fe26803459ff4b2aea6f9b0a06e24
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የመከላከያና የደህንነት አደረጃጀት ህገመንግስቱ ላይ እንደተቀመጠው ባለፉት ሁለት አሰርታት ህዝብን ከማገልገል ይልቅ የወገንተኝነት ፖለቲካ ውስጥ እንደነበሩ ባለፈው ለፓርላማ ንግግር ሲያደርጉ አመላክተው ነበር።
መከላከያ የኢህአዴግ የመጨረሻ ምሽግ?\nቀጥሎም የእነዚህ ተቋማት አሰላለፍ ከመንግስትና ከስርዓት ጋር የሚቀያየር ሳይሆን ወገንተኝነታቸው ለህዝብና ለሃገር ይሆን ዘንድ ማሻሻያ እንደሚደረግባቸውም ተገልጿል። ይህን ተከትሎም የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም የነበሩት ጀነራል ሳሞራ የኑስ በጀኔራል ሳአረ መኮንን፤እንደሁም የቀድሞ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ በጀነራል አደም ሞሃመድ መተካት ሊደረግ የታሰበው ማሻሻያ ጅማሮ ተደርጎ ሊታይ ይችላል። ማሻሻያ ይደረግ ሲባል ከሚነሱ መሰረታዊ ጥያቄዎች መካከል ላለፉት ሁለት አሰርታት ከወገንተኝነት ፖለቲካ የፀዱ አልነበሩም የተባሉት የመከላከያና ደህንነት ተቋማትን ከዚህ መስመር ማውጣት የሚቻለው በምን አይነት ማሻሻያ ነው? የሚለው ቀዳሚው ነው። "መከላከያ የኢህአዴግ የመጨረሻ ምሽግ" የቀድሞ አየር ሃይል አዛዥ የነበሩት ሜጀር ጀነራል አበበ ተክለሃይማኖት ለቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ መከላከያ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው የሚያትት ደብዳቤ ፅፈው ነበር።የኢህአዴግ የመጨረሻ መደበቂያ ነው የሚሉት መከላከያም ሆነ ደህንነቱ ላይ ማሻሻያ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ዛሬም ጥርጥር የላቸውም። "መከላከያ የመጨረሻው የኢህአዴግ ምሽግ ነው።ፀረ ህገመንግስት የሆነ መመሪያም ነበራቸው"በማለት አንዳንድ የመከላከያ ባለስልጣናትም ፖለቲካ ውስጥ መግባታቸውንም ይጠቅላሉ። ማሻሻያው መጀመር ያለበት ረዥም ዓመታትን ያስቆጠረውና ምንም እንኳ ጥሩ ነገሮች ቢኖሩትም በርካታ ችግሮች ያሉበት የአገሪቱ የውጭ ግንኙነትና ደህንነት ፖሊሲን ከማሻሻል መጀመር እንዳለበት ያስረዳሉ። በማንኛውም ዘርፍ የሚደረግ ማሻሻያ ቀላልል እንዳልሆነ ይበልጥ ደግሞ እንደ መከላከያና ደህንነት ያሉ ተቋማት ማሻሻያ ከባድ እንደሚሆን አመልክተዋል። ሁሌም የለውጥ ሂደት ላይ ለውጥ ደጋፊና ተቃዋሚ እንደሚኖር ሁሉ መከላከያና ደህንነትን በማሻሻል ሂደት ውስም በጥላቻና በዘረኝነት ፀረ ለውጥ ሃይሎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ይገምታሉ። ለዚህ መፍትሄ የሚሉት ለለውጥ ሂደቱ የሚወጡ መመሪያዎችም ይሁኑ ሌሎች አቅጣጫዎች ህገ መንግስቱንና ህገመንግስቱን ብቻ የሚከተሉ መሆናቸውን ማረጋገጥን ነው። ከሁሉም በላይ አጠቃላይ የማሻሻል ሂደቱ በባለሙያ በቂ ጥናት ተደርጎበት የሚገባበት ለውጥንና የአገሪቱን ወቅታዊ እውነታ ያገናዘበ እርምጃ መሆን እንዳለበትም ያሳስባሉ። እንኳን እንደ ኢትዮጵያ ባለ ታዳጊ አገር ባደጉ አገራትም የመከላከያና የደህንነት ተቋማት ሁሌም ወደ አንድ ወገን የማዘንበል ነገር የሚታይባቸው በመሆኑ የትኛውም አይነት ሪፎርም ቢደረግ እነዚህን ተቋማት ሙሉ በሙሉ ከወገንተኝነት እንደማያፀዳቸው ያስረዳሉ። ቢሆንም ግን በአገሪቱ የህግ የበላይነትን አረጋግጦ በተቻለ መጠን የተቋማቱ ወገንተኝነት ለህዝብ እንዲሆን ማድረግ እንደሚያስፈልግ ያስረግጣሉ። "ለውጥ አልተጀመረም አልተሞከረምም" በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተወንጅለው በእስር የነበሩትና በቅርቡ በይቅርታ የተለቀቁት እንዲሁም ማእረጋቸው እንዲመለስ የተወሰነው ብርጋዴር ጀነራል አሳምነው ፅጌ መከላከያን ስለማሻሻል ሲታሰብ ዋናው ችግር በወረቀት ላይ የሰፈረው ነገር ሳይሆን በተግባር የሚታየው ነው ይላሉ። ለእሳቸው ይበልጡን ተቋማቱን የሚዘውሩት እነማን ናቸው? የሚለው ጥያቄ ወሳኝ ነው። እሳቸው እንደሚሉት በወሳኝ ወታደራዊ ተቋማት መዋቅር ላይ የሚቀመጡት ሰዎች በቅርፅ ደረጃ ህገመንግስቱን መሰረት አድርጎ የህዝብና የሃገሪቱን ጥቅም ታሳቢ ያደረጉ ቢመስልም የመጡበት የፖለቲካ መስመር ተፅእኖ ግን በተጨባጭ የሚታይ እንደሆነ ይገልፃሉ። በደህንነት ተቋማት በኩል ያለው ነገርም ከዚህ ይለያል ብለው አያምኑም። "የማሻሻያው ጅምር ተደርገው በሚታዩት የቅርብ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
a4e2d85ec2f9ab0ddb982b9d3ac1b537
4bf66622e7496ba6f8a3d947c0cd10f7
የኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ለባለዕድለኞች የሚተላለፍበት ቀን ተራዘመ
የዕጣ አወጣጥ ስርአቱን ተከትሎ የተነሱ የወሰን ይገባኛል ጥያቄን መልስ ለመመለስ እና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት በም/ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ መሪነት የተቋቋመው የወሰን እና የድንበር አጣሪ ቡድን ስራ አለመጠናቀቁ ላለመተላለፉ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የቤቶች እና ልማት ቢሮ ሃላፊ ኢ/ር ሠናይት ዳምጤ ለአዲስ አድማስ  ገልፀዋል፡፡ በርካታ ሰዎች በሚቀጥለው ሳምንት ይተላለፋል የተባለውን መረጃ በመያዝ ቢሯቸው ድረስ በመሄድ እየጠየቋቸው መሆኑን ኢ/ር ሠናይት ገልፀው በእኛ በኩል ያለውን ስራ አጠናቀናል የሚቀረው የኮሚቴው ውሳኔ በመሆኑ በዚህ ቀን ይተላለፋል ለማለት እቸገራለሁ” ብለዋል፡፡ እጣ የወጣላቸው አካላት ቤቶቹ የሚተላለፉበትን ቀን በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቀዋል - ሃላፊዋ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና በኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳድር መካከል ያለውን ወሰን እንዲያጠና የተቋቋመው ኮሚቴ ተግባሩን ባለማጠናቀቁ በሣምንቱ ለባለ እድለኞች ይተላለፋሉ ተብለው የነበሩ የኮዬ ፈጬ የጋራ መኖሪያ ቤትን የማስተላለፊያ ጊዜ መራዘሙ ተገለፀ፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=23333:%E1%8B%A8%E1%8A%AE%E1%8B%AC-%E1%8D%88%E1%8C%AC-%E1%8A%AE%E1%8A%95%E1%8B%B6%E1%88%9A%E1%8A%92%E1%8B%A8%E1%88%9D-%E1%88%88%E1%89%A3%E1%88%88%E1%8B%95%E1%8B%B5%E1%88%88%E1%8A%9E%E1%89%BD-%E1%8B%A8%E1%88%9A%E1%89%B0%E1%88%8B%E1%88%88%E1%8D%8D%E1%89%A0%E1%89%B5-%E1%89%80%E1%8A%95-%E1%89%B0%E1%88%AB%E1%8B%98%E1%88%98&Itemid=180
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
072c1881e6ccbf5e26102f2e834b027c
0cba4d2ba219f4f15f7edb280f108fba
ፌዴሬሽኑ በጅማ አባጅፋር ላይ ውሳኔ አሳለፈ
ከተጫዋቾች የደመወዝ ክፍያ እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር በፌዴሬሽኑ በተደጋጋሚ ውሳኔ ሲሰጥበት የሰነበተው ጅማ አባጅፋር ለሦስት የውጪ ተጫዋቾች የደመወዝ ክፍያን ባለመፈፀሙ ተጨማሪ ውሳኔ ተላልፎበታል።በቅርቡ የክለቡ ነባር ተጫዋቾች በፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ቀርበው የአራት ወራት ደሞዝ አልተከፈለንም በማለት ቅሬታን ያሰሙ ሲሆን ፌዴሬሽኑም የይከፈላቸው ደብዳቤን ለክለቡ ሁለት ጊዜ በመፃፍ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ከዚህም ጉዳይ በተጨማሪ በክለቡ ውል እያለበት የተለያየው አማካዩ ይስሀቅ መኩሪያ ውል እያለብኝ ነው አግባብ ባልሆነ መንገድ የተሰናበትኩት በማለት ባቀረበው አቤቱታ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በተደጋጋሚ ለተጫዋቹ የይከፈለው ደብዳቤን ቢልክም ክለቡ ለመፈፀም ዝግጁ ባለመሆኑ ክለቡን ከኔ አገልግሎት አታገኙም በማለት የእግድ ውሳኔን አስተላልፎም ነበር፡፡አሁን ደግሞ በክለቡ ከሚገኙት ሦስት የውጪ ተጫዋቾች የሰባት ወር እና የአምስት ወራት ደሞዝ ባለመከፈሉ ቅሬታቸውን ያቀረቡ ሲሆን ፌዴሬሽኑም በአስር ቀን ውስጥ ክፍያውን እንዲፈፅምላቸው ውሳኔ በመስጠት ይህን ማድረግ የማይችል ከሆነ ጉዳዩን ወደ ፍትህ አካላት እንደሚወስደው እና ተጫዋቾቹ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል ቢኖራቸውም መልቀቂያ ደብዳቤን እንደሚሰጥ በደብዳቤው ገልጾ ለክለቡ ልኳል፡፡የጅማ አባጅፋር ስራ አስኪያጅ አቶ ሱልጣን ቶፊቅ በጉዳዩ ዙርያ ለሶከር ኢትዮጵያ እንደገለፁት ከሆነ “ለሁሉም ተጫዋቾች የወር ደሞዛቸውን ጠብቀን እየከፈልን ነው ያለነው። የሚቀረው የግንቦት እና ሰኔ ወር ብቻ ነው። እሱንም በሂደት እንከፍላለን።” ያለለ ሲሆን ሦስቱ ተጫዋቾች ማለትም ኦኪኪ አፎላቢ (አሁን መቐለ) ዲዲየር ለብሪ (አሁን ስሑል ሽረ) እና ከባህርዳር ጋር ስሙ የተያያዘው ተከላካዩ አዳማ ሲሶኮ በክለቡ ውል እንዳለባቸው፣ የወሰዱትን ንብረት እንዳልመለሱ እንዲሁም እስካሁን በአካል መጥቶ መልቀቂያ የጠየቀ ተጫዋች እንደሌለ ገልፀዋል፡፡የተጫዋቾቹ ወኪል የሆነው ኤርሚያስ አሸኔ በበኩሉ የፊፋን ህግ በመጥቀስ “ተጫዋቾቹ ሁለት ወር ደሞዝ ካልተከፈላቸው በህጉ መሠረት ክለቡ ተጫዋቾቹን የመልቀቅ ግዴታ አለበት። ያን ካላደረገ ግን ፌዴሬሽኑ ራሱ መልቀቂያቸውን ይሰጣል።” ብሏል። ለተጫዋቾቹ ክፍያ እየተፈፀመላቸው ለተባለውም አንድም ገንዘብ በተጫዋቾቹ አካውንት ውስጥ እንዳልገባ ተናግሯል፡፡*ለጅማ አባጅፋር ፌድሬሽኑ የላከው ደብዳቤ ይህንን ይመስላል፡-
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/51064
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
4149dc7350493294e6235264f8301950
f220eb788ce4ab8a164ebc475cc7e33e
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሌሎች አየር መንገዶች የአክሲዮን ድርሻ ሊሸጥ እንደሚችል ገለጸ
የግል ድርጅቶች ድርሻ መግዛት ቢፈልጉ በአየር መንገዱ ግሩፕ ኩባንያዎች እንደሚስተናገዱ ተጠቁሟልየኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የአክሲዮን ድርሻ በከፊል በመሸጥ ወደ ግል የተወሰኑ ድርሻዎችን ለትልልቅ የአፍሪካ አየር መንገዶች ማስተላለፉ እንደማይቀር ይፋ አደረገ፡፡ በእንግሊዝ ሳምንታዊ በረራውን ወደ 11 ያሳደገበትን የማንቸስተር ከተማ መዳረሻ ይፋ አድርጓል፡፡ የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም ሪፖርተር ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በሚገኙ በርካታ አየር መንገዶች ውስጥ በከፊልና ሙሉ በሙሉ ድርሻ እየገዛ በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ በመሆኑም እንደ ትልልቅ የሚባሉት ደቡብ አፍሪካ ያሉ አየር መንገዶች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የባለቤትነት ድርሻ ለመግዛት ጥያቄ ካቀረቡ ሊስተናገዱ እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡ ከወራት በፊት በተላለፈው በኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውሳኔ መሠረት በከፊል ይዞታቸው ወደ ግል ይዛወራሉ ከተባሉት ውስጥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ውሳኔውን ተከትሎም አየር መንገዱ በምን አግባብ የአክሲዮን ድርሻዎችን ለውጭ ኩባንያዎች እንደሚሸጥ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ያስረዱት አቶ ተወልደ፣ ዝርዝር ጉዳዮቹ በሒደት እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡ይሁንና የአክሲዮን ሽያጩ በሁለት መንገድ እንዲከናወን መታቀዱንም ጠቁመዋል፡፡ አንደኛው ትልልቅ የሚባሉት አየር መንገዶች ጥያቄ በሚያቀርቡበት ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለድርሻ የሚሆኑበት መንገድ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ሌሎች የግል ባለሀብቶችና ኩባንያዎች ፍላጎት ካላቸው በሌሎች የአየር መንገዱ ኩባንያዎች ውስጥ ባለድርሻ የሚሆኑበት አካሄድ መታሰቡን አብራርተዋል፡፡ አየር መንገዱ በቅርቡ ከዲኤችኤል ጋር ስምምት ባደረገበት በሎጂስቲክስ ዘርፍ፣ በሆቴልና በምግብ ዝግጅት፣ በአቪዬሽን አካዴሚው፣ በካርጎ፣ የግራውንድ አገልግሎት፣ በኤሮስፔስ ማኑፋክቸሪንግና በሌሎችም ዘርፎች የሚንቀሳቀሱ ኩባንያዎቹ ውስጥ እንዲሳተፉ ሊያደርግ የሚችልበት አግባብ እንደሚኖር ተብራርቷል፡፡ ይህ ቢባልም የኩባንያውን የሀብት ግመታና መሰል ሥራዎች ማከናወን ገና እንዳልተጀመረ ከአቶ ተወልደ ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡  የአየር መንገዱ ድርሻ ለአገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ባለሀብቶች በከፊል ይሸጣል የሚለው ውሳኔ ከጅምሩ በመንግሥት ላይ የሰላ ትችት ማስከተሉ ይታወሳል፡፡ ባለሙያዎች በአየር መንገዱ ላይ የተላለፈው ውሳኔ እንዲጤን ሲወተውቱ ሰንብተዋል፡፡ የኢኮኖሚ ባለሙያዎቹ አቶ ዘመዴነህ ንጋቱና ኢዮብ ተስፋዬ (ዶ/ር) አየር መንገዱ እንደ ሌሎች የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ታይቶ ይሸጥ መባሉን ከማይቀበሉትና መንግሥት ውሳኔውን መልሶ እንዲፈትሽ ከሚያሳስቡት መካከል የሚጠቀሱት ግንባር ቀደሞቹ ናቸው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከሰኞ ታኅሳስ 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ሁለተኛው መዳረሻ በሆነው የማንቸስተር ከተማ በሳምንት አራት ቀናት መብረር የጀመረበትን ሥነ ሥርዓት አየር መንገዱ አከናውኗል፡፡ ላለፉት 46 ዓመታት በእንግሊዝ ለንደን ከተማ ተወስኖ የቆየው የበረራ አገልግሎት ማንቸስተር ከተማን በማካተቱ በሳምንት የነበረውን የሰባት ቀናት በረራ ወደ 11 ከፍ አድርጎታል፡፡ የማንቸስተር በረራው በአሁኑ ወቅት በብራሰልስ በኩል ለጊዜው እንደሚከናወን ያስታወቁት አቶ ተወልደ፣ ወደፊት በቀጥታ መብረር እንደሚጀመር አስረድተዋል፡፡በአፍሪካ ከ60 በላይ መዳረሻዎች ያሉት አየር መንገዱ፣ በአፍሪካ 80 በመቶ የአየር ትራንስፖርት ከተቆጠሩት የውጭ ኩባንያዎች ማለትም ከኤምሬትስ፣ ከኢትሃድ፣ ከተርኪሽና ከሌሎችም ትልልቅ አየር መንገዶች ጋር በመፎካከር ላይ ይገኛል፡፡ በመላው ዓለም 118 መዳረሻዎች ያሉት አየር መንገዱ በመጪው ሳምንት ወደ ሞስኮ መብረር እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ ወደ ፈርንሣይ ማርሴይ ከተማ በረራ ለመጀመር ድርድር እያካሄደ እንደሚገኝና ፈቃድ ለማግኘት መቃረቡን አቶ ተወልደ አስታውቀዋል፡፡ ለአፍሪካ መንገደኞች ዋናው የአየር ትራንስፖርት አቅራቢ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከደንበኞቹ ውስጥ ከ70 በመቶው በላይ የትራንዚት መንገደኞች በመሆናቸውም ጭምር የአፍሪካ መንገደኞችን ከተቀረው ዓለም ጋር የማገናኘቱ ተግባር ላይ ከፍተኛ ውድድር እንዳለበትም አስታውቋል፡፡በአሁኑ ወቅት ከጋና፣ ከዛምቢያ፣ ከኮትዲቯር፣ ከማሊ፣ ከሩዋንዳ፣ ከቡርኪና ፋሶ እንዲሁም በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ከሞዛምቢክ አየር መንገድ ድርሻ በመግዛት በባለቤትነት እያስተዳደረ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከ110 በላይ አውሮፕላኖችን በማሰማራት በሁለተኛ ደረጃ ከሚከተለው የግብፅ አየር መንገድ (69 አውሮፕላኖች አሉት) በብዙ ርቆ በአፍሪካ ቀዳሚው በመሆን ይመራል፡፡
ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/article/14148
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
2ea4ff97596d81e00609b71ceaf1fac3
674cd2a2511da8cbaee144f3b4730e4a
ከ98 ቤቶች በስተቀር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕግድ ተነሳ
የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ.ም. ዕጣ ወጥቶባቸው የነበሩና በፍርድ ቤት ዕግድ ተጥሎባቸው ከነበሩት ከ18 ሺሕ በላይ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ከ98 ቤቶች በስተቀር በቀሪዎቹ ላይ የተጣለው ዕግድ ተነሳ፡፡ ዕጣው ከወጣ በኋላ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የፈጸሙት መቶ በመቶ ክፍያ ውል ታልፎ ቅድሚያ ለእነሱ በዕጣ መሰጠት እየተገባ፣ ሁሉንም ተመዝጋቢዎች በማካተት የከተማ አስተዳደሩ ዕጣ ማውጣቱን በመቃወም 98 ግለሰቦች ክስ መመሥረታቸው ይታወሳል፡፡   ተከሳሾቹ ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ እንዳስረዱት፣ በተመዘገቡበት ወቅት እንደተነገራቸው ለቤቶቹ የተገመተውን ዋጋ ሙሉ በሙሉ በአንድ ጊዜ መክፈል ከቻሉ፣ ዕጣ የሚወጣው በእነሱ መካከል ብቻ ለማወዳደር መሆኑን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የፈጸሙት ውል ያስረዳል፡፡ነገር ግን የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ40 በመቶ በላይ የቆጠቡ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተመዝጋቢዎችን በማካተት፣ ከ18 ሺሕ በላይ ቤቶች ዕጣ ተወዳዳሪ አድርጓቸዋል፡፡ የዕጣ አወጣጡን ሥርዓት በመቃወም ግንባታ የሚያካሂደውን ቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ፣ የኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ሚኒስቴርን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በመክሰሳቸው፣ ዕጣ የወጣባቸው ከ18 ሺሕ በላይ ቤቶችና በቀጣይ ዕጣ የሚወጣባቸው ቤቶች ዕግድ እንዲጣልባቸው አድርገዋል፡፡ ከሳሾቹ 98 ግለሰቦች ሲሆኑ፣ ያቀረቡትን ክስ በመቃወም የአስተዳደሩ ቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርቧል፡፡ በተጨማሪም ለሚደርሰው ኪሳራ ገንዘብ እንዲያሲዙ ጠይቆ፣ ገንዘቡ ምን ያህል እንደሆነ ዝርዝር ማስረጃ እንዲያቀርብ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ስምንተኛ ቀጥተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት ለግንቦት 19 ቀን 2011 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር፡፡የሪፖርተር ምንጮች ማረጋገጥ እንደቻሉት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባሳለፈው ውሳኔ የመብት ጥያቄ ያነሱት ግለሰቦች መቶ የማይሞሉ ሆኖ ሳለ፣ ከ18 ሺሕ በላይ ቤቶች መታገዳቸው ተገቢ ባለመሆኑ ፍርድ ቤቱን በማነጋገር የተሻሻለ ውሳኔ እንደሚያሰጥ አቅጣጫ ማስቀመጡ ታውቋል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ግንቦት 19 ቀን 2011 ዓ.ም. በዋለው ችሎት ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ በሰጠውም ትዕዛዝ የከሳሾች ቁጥር 98 ሆኖ ሳለ ከ18 ሺሕ በላይ ቤቶችን ማገድ ተገቢ ስላልሆነ፣ ክስ በመሠረቱት 98 ሰዎች ቁጥር ከየሳይቱ ዕጣ በወጣባቸው የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ከሁሉም ዓይነት ዕግዱ እንዳለ እንዲቆይና የቀሪዎቹ ቤቶች ዕግድ እንዲነሳ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ አስተዳደሩም ከሳሾች እንዲያስይዙ በጠየቀው የገንዘብ መጠን ላይ ማሻሻያና ዝርዝር የሚቀርብ ከሆነ፣ ለመጠባበቅ ለግንቦት 28 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡   
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/article/15762
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
726e3ae025016a572d909b69f44ef3de
c81e0bf3c976c2d20005521ee6e8014f
ታንዛንያ ወደቧን በ154 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለማስፋፋት ከቻይና ጋር ተስማማች
ታንዛኒያ የሀገሪቱን ዋና ወደብ ለማስፋፋት የ154 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኮንታራት ከቻይና ኩባንያ ጋር መስማማቷን አስታወቀች ።     ስምምነቱ የወደቡን አቅም በማሳደግ ሀገሪቱንና የወደቡ ተጠቃሚ ሃገራትን የወጭና ገቢ ንግድ ለማጠናከር የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ የታንዛንያ ዳሪሰላም ወደብ በምስራቅ አፍሪካ በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ ወደቦች አንዱ ነው፡፡ይህን ወደብ የሀገሪቱ መንግስት ለማስፋፋት የያዘውን ዕቅድ ግብ እንዲመታ የብድር አቅርቦት ለማግኘት የዓለም ባንክን ብድር ቀደም ሲል  ተጠይቆ ነበር ፡፡እናም የዓለም ባንክ ለወደቡ ማስፋፊያ የሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር  የብድር አቅርቦት ባለፈው ጥር ወር ለታንዛኒያ መንግስት ፈቅዷል፡፡የአሁኑ የ154 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ስምምነት ደግሞ ከዓለም ባንክ ድጋፍ ውጭ ከቻይናው ሃርበር ኢንጅነሪንግ  /ሲ.ኤች.ኢ.ሲ / ጋር የተደረገ የገንዘብ ድጋፍ  ነው፡፡ግንባታውንም የቻይናው ኮሚዩኒኬሽን ኮርፖሬሽን ኩባንያ የሚያከናውነው ይሆናል፡፡ይህ ከፍተኛ የንግድ መዳረሻ የሆነውን የዳሬ ሰላም ወደብ ማስፋፊያ መደረጉን ተከትሎ የሀገሪቱን ወጭና ገቢ ንግድ በማቀላጠፍ ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡የታንዛኒያ የአሁኑ የወደብ የማስፋፊያ እቅድ ሀገሪቱ በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ያለውን የትራንስፖርትና የንግድ እንቅስቃሴ ማዕከል እንድትሆን ለማድረግ ያሰበችውን  ማሳያ እንደሆነም ነው የተነገረው፡፡የታንዛኒያ ወደብ ማስፋፊያ  ሲጠናቀቅ በአሁኑ ወቅት ወደቡ እያስተናገደ ያለውን የ20 ሚሊዮን የኮንቴነር ብዛት ወደ 28 ሚሊዮን የማሳደግ አቅም ይኖረዋል፡፡በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና  ግዙፍ ኢኮኖሚ ከሚያንቀሳቅሱ ሃገራት ተርታ የምትጠቀሰው ታንዛኒያ ያላትን የወደብ ሃብት፣የባቡር ትራንስፖርት አቅሟን በማጠናከርና የየብስ መንገዶችን በማጎልበት ወደብ አልባ የሆኑ የቀጠናው ሃገራት እያሳዩት ያለውን የምጣኔ ሃብት ዕድገት ለመጠቀም አልማለች፡፡ለዚህ ማሳያ ደግሞ በታንዛኒያ፣በኬንና ኡጋንዳ የተገኘውን  ከፍተኛ የነዳጅ ክምችት በርካታ በነዳጅ ማውጣት ዘርፍ ያሉ ኮባንያዎች ልባቸው ወደ ምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ቀልባቸው እንዲሸፍት እያደረገ ነው፡፡እናም ይህን ሃብት ለማጓጓዝ የሚያስችል የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ባለመደረጉ ሀገራቱ ካላቸው ሃብት መጠቀም ያልቻሉ በመሆናቸው ታንዛንያም በቀጣይ ክፍተቱን ለመሙላት  እንደምትሰራ አስታውቃለች፡፡    አሁን ከዓለም ባንክ እና ከቻይናው ሃርበር ኢንጅነሪንግ በተገኘ ብድር እንዲሁም በሃገሪቱ መንግስት የዳሬሰላም ወደብ ማስፋፊያ የሚደረግለት ይሆናል፡፡ በምስራቅ አፍሪካ የዚህ ወደብ ተቀናቃኝ የሆነው የኬንያው የሞምባሳ ወደብ ፤ ወደብ አልባ ለሆኑ የአፍሪካ ሀገራት እያገለገለ ይገኛል፡፡እኤአ በ2014 የዓለምባንክ ባወጣው ሪፓርት እንዳመላከተው የገቢ እቃዎችን ለማስተናገድ የዳሪሰላም ወደብ አቅሙ አናሳ በመሆኑ ምክንያት ታንዛኒያንና ተጎራባች ሃገራትን በዓመት እስከ 2.6 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጭ እንዲያደርጉ እያስገደዳቸው ነው፡( ምንጭ:   ሮይተርስ )
ቢዝነስ
https://waltainfo.com/am/32830/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
2dc140219708160d6377346ff61a137a
1adbb0c8d099f9c6b1a4a7cae4e38742
ምድራችን ላይ እስትንፋስ ያለው ሁሉ ሕልውናው የአንዱ ከሌላኛው ጋር የተሳሰረ ነው።
ብዝኀ ሕይወት ምንድን ነው? ለምንስ ግድ ይሰጠናል?\nበዓለም ላይ የተለያዩ ፍጥረታት አንዳቸው ከሌላቸው ጋር በሰመረ ጥምረት ይኖራሉ። አንዳቸው ከሌላቸው ጋር ያላቸው መስተጋብር እንዲሁም ከሚኖሩበት አካባቢ ጋር ያላቸው ግንኙነትም የተጣጣመ ነው። የሰው ልጅም በዚህ የሕይወት ዑደት ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ ሕይወቱም በዓለማችን ላይ ከሚገኙ ፍጥረታት መኖር ጋር የተሳሰረ ነው። • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በቅርበት የተከታተሉት የእራት ግብዣ • ህወሀት እና ህግደፍ ይታረቁ ይሆን? ብዝኀ ሕይወት ምንድን ነው? ሕይወት ያለው ሁሉ፣ እኛን ጨምሮ፣ በሚኖርበት ፕላኔት ላይ በዙሪያው የተለያዩ ሕይወት ያላቸው ነገሮች ሊኖሩ ይገባል። ይህንን ነው ብዝኀ ሕይወት የምንለው። ተክሎች የምንተነፍሰውን አየር ያመርቱልናል፤ ንቦች ደግሞ ሰብሎች እንዲራቡ በማድረግ ውስጥ አይተኬ ሚና አላቸው። ፈንገስ ደግሞ አፈር ለምነቱን ጠብቆ አንዲቆይ ያደርጋል። ስለዚህ ካልተበረዘው የተፈጥሮ ዓለም፣ የምንጠጣውን ኩልል ያለ ንፁህ ውሃ፣ ባመመን ጊዜ የምንፈወስበትን መድኀኒት እንዲሁም መንፈሳችንን የሚያድስ እይታ እናገኛለን። ከምድር ገፅ ላይ የአንድ ተክል ወይም እንስሳ ዝርያ መጥፋት ቀላል ሊመስል ይችል ይሆናል። ነገር ግን አንዳችን ከሌላችን ጋር በማይበጠስ ገመድ ስለተሳሰርን የአንድ ዝርያ መጥፋት ትልቅ ጉዳት ነው። ስለምን ግድ ይሰጠናል? አንድ ቤትን አስቡ። እናም አንድ ሰው ቤቱ ከተገነባበት ጡብ አንዱን መዞ ቢያወጣው ቤቱ ውበቱ እየደበዘዘ ጥንካሬውም እየደከመ ይሄዳል። በርካታ ጡቦች ሲወጡ ደግሞ በአጠቃላይ ቤቱ ይፈርሳል። በምድርም ከአጠቃላይ የሕይወት ማዕቀፉ ውስጥ አንድ ዝርያ ሲጎድል፤ ብዝኀ ሕይወቱ ደካማ እየሆነ ይሄዳል፤ ያ ደግሞ በምድር ላይ ሕብር ሠርተው እየኖሩ ያሉ ፍጥረታትንም ያያደክማል። በአሁኑ ወቅት ዓለማችንን ስንመለከት መፃዒ ተስፋችን ጭጋግ የለበሰ ነው። ተፈጥሮ ሚዛኗ ተዛብቷል። ምን እየሆነ ነው? ለምን? ተመራማሪዎች በምድራችን ላይ የተለያዩ ዝርያዎች በሚሊየን ዓመታት አይተን በማናውቀው ፍጥነት እየጠፉና እየተመናመኑ ነው ይላሉ። ይህንን እያደረገ ያለው ደግሞ የሰው ልጅ ነው። የደን መጨፍጨፍ፣ ለእርሻ፣ ለቤት ግንባታና ኢንደስትሪን ለማስፋፋት ተብለው የሚካሄድ ምንጣሮና ቃጠሎ ምድራችንን አደጋ ላይ ጥለዋታል። አየሩን፣ አፈሩን እና ውሀውን እየበከልን በእነዚህ ላይ ኑሯቸውን ያደረጉ ፍጥረታትን አደጋ ላይ ጥለናል። ሕገ ወጥ የዱር እንስሳት ንግድና አደን፣ ከተገቢው በላይ አሳ ማስገር እንስሳት በከፍተኛ ቁጥር እንዲሞቱና እንዲጠፉ እያደረገ ነው። የሰው ልጅ እፅዋትንና እንስሳትን ከዚህ ቀደም ወደማይገኙበት የዓለማችን ክፍል እያጓጓዘ፤ በስፍራው ቋሚ ነዋሪ የነበሩት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳረፈባቸው ይገኛል። • ለወሲብ ባርነት ወደ ቻይና የሚወሰዱት ሴቶች በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ የአየር ጠባይ ለውጥ ምድራችንን እያናወጣት ነው። ይህ ሁሉ ጥፋት ተስፋችን የተመናመነ ሊያስመስለው ይችላል። ግን ተስፋ አለን። እያንዳንዱ ግለሰብም ሆነ አገራትን የሚመሩ ባለስልጣናት ማድረግ የሚችሉት ነገር አለ። መንግሥታት ሕገ ወጥ አደንንና የዱር እንስሳት ንግድን ቢከላከሉና ዝርያቸው ለመጥፋት ለተቃረቡ እንስሳት ልዩ ጥበቃ ቢያደርጉ ተፈጥሮን መታደግ እንደሚቻል ባለሙያዎች ይመክራሉ። ምን እናድርግ? ማድረግ የምንችለው ነገር አለ። የምንጠቀመውን ኃይል መቀነስ፣ ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ እንዲውል በማድረግ በመጠቀም፣ አየርንና ምድሪቱን ከብክለት መታደግ፣ ነዳጅ በመቀነስ ሌሎች የኃይል አማራጮችን መጠቀም። ከባቢ አየሩን የማይጎዱ ምርቶችን መጠቀምም ልናደርጋቸው ከምንችላቸው ነገሮች መካከል ይገኝበታል። በሚኖሩበት አካባቢ አበባ በመትከል ንቦች...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
83ee5549be5bb11299b611194b006756
f468dc2ee283866b65086ab18aca9870
አዋይ
አዋይ ከቤት ጋር በብዛት የሚያያዝ የመንፈስ አይነት ነው። ከቦታም ጋር ሊያያዝ ይችላል። ሴትም ሆነ ወንድሊሆን ይችላል። አንድ አንድ የኢትዮጵያ ሰዎች ለቤቱ አዋይ በማለት ምግብ በባዶ ጠረጴዛ ላይ ሲተው ይስተዋላሉ ። ማጣቀሻ መንፈስ የአዕምሮ በሽታ
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
4560e7ce300890594b6db32511d01cfc
7d6e80dddfe1a106daaed27c215a6ebb
ስሑል ሽረ አዲስ አሰልጣኝ ቀጠረ
በዚህ ሳምንት ከአሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ጋር በስምምነት የተለያዩት ስሑል ሽረዎች ሲሳይ አብርሀምን አዲስ አሰልጣኝ አድርገዋል።ከዚህ በፊት በአክሱም ከተማ፣ አዳማ ከተማ፣ ሼር ኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ታዳጊ ብሄራዊ ቡድን ያሰለጠኑት አዲሱ አሰልጣኝ ባለፈው ዓመት በዚህ ወቅት ከአዳማ ከተማ ጋር በስምምነት ከተለያዩ ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ክለብ ሥራ የሚመለሱ ይሆናል።ቀደም ብለው ዮናታን ከበደን ያስፈረሙት ስሑል ሽረዎች በአጥቂው ሳሊፍ ፎፋና ምትክ አጥቂ ያስፈርማሉ ተብሎ ይጠበቃል።©ሶከር ኢትዮጵያ
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/56947
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
272995e5fab1325ea6b6c6e62513a279
933ff3b9320fb047aedb3d1cf1515f0b
ቺ ዮው
ቺ ዮው በቻይና፣ በና በህሞንግ አፈ ታሪክ በኩል ጥንታዊ ንጉሥ ነበረ። በትውፊቱ መሠረት ቺ ዮው 2365 ዓክልበ. ግድም የሊ ወገን ንጉሥ ሲሆን የያንዲና የኋንግዲ ጠላት ሆነ። ሦስት ውግያዎች ተከተሉ። በመጀመርያው የቺ ዮው ሥራዊት ያንዲውን አሸነፈው። ከዚያ ያንዲው ተሸንፎ ወደ ኋንግ ዲ (ወደ ዥዎሉ) ሸሸ። በሁለተኛው የዥዎሉ ውግያ ኋንግ ዲ እና ቺ ዮው ተጋጠሙ። በዚህ ውግያ ቺ ዮው ጉምን በጥንቆላ ፈጥሮ ኋንግ ዲ እንደገና በተነው፣ ብዙም ሌሎች ጉድ ሥራዎች እንደ ተከሠቱ የሚል ወሬ አለ። በቻይና መዝገቦች ዘንድ፣ ቺ ዮው በዚህ ውግያ ድል ሆነ። በኮርያ መጻሕፍት ግን ቺ ዮው («ጃውጂ ኋኑንግ» ተብሎ) በዚህ ውግያ ድል አደረገ፣ ደግሞ የሺንሺ ንጉሥ ይባላል። በቻይና ሃይማኖት ደግሞ ከ200 ዓክልበ. እስከ 65 ዓ.ም. ግድም ድረስ ቺ ዮው እንደ ጦርነት አምላክ ይቆጠር ነበር። የቻይና አፈ ታሪክ ኮሪያ
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
4cd7bb91c0123f1d391afd650039a4f8
2ad92622af772da3c9fb9466adce2013
የኢኳቶሪያል ጊኒ ፕሬዝዳንት ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
የኢኳቶሪል ጊኒ ፕሬዚዳንት ኦቢያንግ ኑጌማ ማሶጎ አዲስ አበባ ገብተዋል።ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፥ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል።በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታም ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ከአፍሪካ ህብረት አመራሮች ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል።በነገው ዕለትም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘውን የፆሬ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያን እንደሚጎበኙ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።ከዚህ ባለፈም የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የስደተኞች ስምምነት የተፈረመበትን 50ኛ ዓመት አስመልክቶ በአፍሪካ ህብረት በተዘጋጀ ፕሮግራም ላይ ይሳተፋሉ።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/31190/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
ff2755b513d04d66d0da8d34931fd794
26cbff7725d05d747463b2bdba22c5a5
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትህነግ በከፈተው ጦርነት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የምግብና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትህነግ በከፈተው ጦርነት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የምግብና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 14/2013 ዓ.ም (አብመድ) ከተማ አስተዳደሩ ለመከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኀይልና ሚሊሻ በሕግ ማስከበር ርምጃው ላሳየው ተሳትፎም አድናቆቱን ገልጿል፡፡ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰለሞን ፍስሃ 3 ሺህ ኩንታል ጤፍ፣ ስንዴና በቆሎ ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል፡፡በአማራ ክልል ካሁን ቀደም ተመሳሳይ ድጋፍ ከከተማ አስተዳድሩ ማድረጉንም አስታውሰዋል፡፡ በቀጣይም ተደጋግፈን የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል እንሰራለን ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፡፡ድጋፉን የተረከቡት የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ፋንታ ማንደፍሮ (ዶክተር) እንደተናገሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ያደረገው ድጋፍ ለሌሎች አርዓያ የሚሆን ነው፤ ለተደረገው ድጋፍም በክልሉ ሕዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%a8%e1%8a%a0%e1%8b%b2%e1%88%b5-%e1%8a%a0%e1%89%a0%e1%89%a3-%e1%8a%a8%e1%89%b0%e1%88%9b-%e1%8a%a0%e1%88%b5%e1%89%b0%e1%8b%b3%e1%8b%b0%e1%88%ad-%e1%89%b5%e1%88%85%e1%8a%90%e1%8c%8d-%e1%89%a0/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7eab6be6513d07111bf61b503d288980
ce38fed03fee1ca9450104c77cdee18a
"የቻይናን ኃያልነት ለመግታት ረፍዷል"
አርቲስትና የፊልም ባለሙያ አይዌይዌይ "የምዕራቡ አለም ስለ ቻይና መጨነቅ የነበረበት ከአስርት አመታት በፊት ነበር። በአሁኑ ሰዓትም ግን ረፍዷል። ምክንያቱም ምዕራባውያን ከቻይና ጋር ጠንካራ ስርአት ዘርግተዋል ዝም ብለው ቢያቋርጡትም በከፍተኛ ሁኔታ ይጎዳሉ። ለዚያም ነው ቻይና የእብሪተኛ ባህርይ የምታሳየው" ብሏል። በ2008ቱ የቤጂንግ ኦሎምፒክስ የወፍ ጎጆ ስታዲየምን ዲዛይን ያደረገው አርቲስቱ የቻይናን መንግሥት መተቸቱንም ተከትሎ ነው ከባለስልጣናቱ ጋር ችግሮች መፈጠር የጀመሩት። በ2015ም ቻይናን ለቆ በበርሊን ኑሮውን አድርጎም ነበር። በአሁኑ ሰዓት ደግሞ መኖሪያውን ካምብሪጅ አድርጓል። አይ ዌይዌይ እንደሚለው በአሁኑ ወቅት ቻይና ያላትን የምጣኔ ኃብት ኃያልነት ለፖለቲካዋ ተፅእኖም ትጠቀምበታለች። በቅርብ አመታት የቻይና የፖለቲካ ተፅእኖ በጉልህ መታየት ጀምሯል። እየጨመረ የመጣው ተፅእኖ ከአስር አመታት በፊት የነበረችው ቻይና ልታይ ልታይ የማትልና፣ ድምጿም በአለም ጎልቶ አይሰማም ነበር። የመንግሥት ባለስልጣናቷም ይዘውት የነበረው መፈክርም "ብርሃንን ደብቆ ጊዜን መግዛት" የሚል ነበር። በርካታ ሚኒስትሮቿም ቻይና አሁንም ቢሆን ታዳጊ አገር ናት ከምዕራቡ አለምም ብዙ መማርን ትሻለች ሲሉም ይሰሙ ነበር። ሆኖም የዢ ሺንፒንግ ወደ ስልጣን መምጣት ቻይና በአለም ታሳየው የነበረውን ባህርይ ሙሉ በሙሉ ቀየረው። በ2012 ዢ ሺንፒንግ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ዋና ፀሃፊ ሆኑ፣ በቀጣዩ አመት ፕሬዚዳንት ዢ ሺንፒንግ ቻይና በአለም ላይ ያላትን ቦታም ሆነ ገፅታ በአዲስ መልክ ያዋቀሩ ናቸው ይባልላቸዋል። የአገሪቷም መፈክር "ለስኬት እንስራ" በሚል ተተካ። በሆነ መንገድ ቻይና አሁንም ቢሆን ታዳጊ አገር ናት ምክንያቱ 250 ሚሊዮን ህዝቦቿ ከድህነት ወለል በታች ስለሚገኙ። በአለም ላይ ሁለተኛ ታላቅ የምጣኔ ኃብት ባለቤት ናት። በአሁኑም ወቅት አሜሪካን የምትገዳደራትና በቀጣዩ አመታትም ትቀድማታለችም ተብሎ የምትጠበቅም ሃገር ናት፣ ቻይና። ቻይና በአለም ላይ ያላት ተፅእኖ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ እየታየ ነው። በተቃራኒው ኃያሏ አገር አሜሪካም በሚታይ መልኩ ተፅእኖዋ እያሽቆለቆለ ነው። የቻይና ግሎባል ታይምስ ጋዜጣ አዘጋጅ ሁ ሺን ቻይና በፖለቲካው ላይ ያላት ተፅእኖና ጫና በመላው አለምም እየተንሰራፋ ነው። ከጫፍ ጫፍ በሚባል ሁኔታ ከግሪላንድ፣ ካሪቢያን ደሴቶች፣ ፔሩ፣ አርጀንቲና፣ ፓኪስታን፣ ሞንጎሊያ የቻይና እጅ የሌለበት የለም። በቅርቡም የካሪቢያኗ ባርቤዶስ ደሴት የእንግሊዟን ንግሥት በርዕሰ ብሄርነት አንፈልጋቸውም ማለቷን ተከትሎ የእንግሊዙ የፓርላመንት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ቻይና ናት ሃሳቡን ያመጣችው በማለት ወቅሰዋታል። ቻይና በአለም ላይ ያላት ተፅእኖ በዚህ ተመለስ የሚባል አይደለም፤ በብሄራዊ ፍላጎቷ የሚመጣንም አገር ዝም ብላ አታልፈውም። የቲቤት መንፈሳዊ መሪ ዳላይ ላማ በቅርቡ ለንደንን መጎብኘታቸውን ተከትሎ የእንግሊዝና የቻይና ግንኙነት በተወሰነ መልኩ ሻክሮ ነበር። በቅርቡም የቼክ ሪፐብሊክ ፓርላማ አፈ ጉባኤ ታይዋንን መጎብኘታቸውን ተከትሎ፣ ከፍተኛ ዲፕሎማት አስጠንቅቀዋል። ግልፅ በሆነ መልኩ ቻይናን ለመተንኮስም ሆነ ከጀርባቸው ሆነው የሚያሴሩ የፀረ- ቻይና ኃይሎችን አገራቸው እንደማትታገስና የሚከተለው ነገር ክፉ ይሆናል ብለዋል። የቻይናና የሌሎች አገራት ፍጥጫ ምንም እንኳን አንዳንዶች ቻይና ያላትን ምጣኔ ኃብት በመጠቀም ከፍተኛ ተፅእኖም ታሳርፋለች ቢሉም ተናጋሪውና ተፅእኖ ፈጣሪው የቻይና ግሎባል ታይምስ ጋዜጣ አዘጋጅ ሁ ሺን አይስማማም። ቻይና አገራትን እያብረከረከች ነው የሚለውም ተቀባይነት የለውምም ይላል። "አንድ መጠየቅ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
5612ef1f0486827336ec607059ed7759
e7a21334f893b0b82235fe3337dcbc91
የድሬዳዋ ከተማ ቡድን አባላት ከፍተኛ ድጋፍ አደረጉ
ብርቱካናማዎቹ ለኮሮና ወረርሺኝ መከላከያ የሚሆን የአንድ ወር ደሞዛቸውን ለግሰዋል።የክለቡ ተጫዋቾችን ጨምሮ መላ አባላትን ያሳተፈው እና 1,000,061 (አንድ ሚልዮን ስልሣ አንድ ሺህ) የሚገመተውን ድጋፍ ያደረጉት ብርቱካናማዎቹ በቀጣይ ቀናትም በግንዛቤ ማስጨበጥ እና ከክለቡ ማኅበረሰብ ድጋፎችን በማሰባሰብ እንደሚቀጥሉ ለማወቅ ተችሏል።የእግርኳስ ማኅበረሰቡ በዓለም አቀፍ ደረጃ አሳሳቢ የሆነው ወረርሺኝን ለመከላከል የገንዘብ እና የቁሳቁስ ድጋፎች ከማድረግ አልፎ በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን ግንዛቤ በማስጨበጥም የሚመሰገን ተግባር እየፈፀመ ይገኛል።© ሶከር ኢትዮጵያ
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/57577
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
208ce32a595a91c060db8919bb9c5981
92e012153715603660cbd148da19fa5a
በብሔራዊ ደህነንት ምክር ቤት በተዘጋጀ የምርጫ ፀጥታ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 18 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት በተዘጋጀው አገር አቀፍ የምርጫ ፀጥታ ዕቅድ ላይ የፌዴራልና የክልል ባለድርሻ አካላት ተወያዩ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%89%a5%e1%88%94%e1%88%ab%e1%8b%8a-%e1%8b%b0%e1%88%85%e1%8a%90%e1%8a%95%e1%89%b5-%e1%88%9d%e1%8a%ad%e1%88%ad-%e1%89%a4%e1%89%b5-%e1%89%a0%e1%89%b0%e1%8b%98%e1%8c%8b%e1%8c%80-%e1%8b%a8/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8e7662e1f307a79f71b9fa6386ba024a
4603ea17255885bbf4c81680bcbe272d
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የቻይና ጉብኝታቸውን አጠናቀው አሰብ ገቡ
ሰሞኑን በቻይና አፍሪካ የትብብር ፎረም ቻይና የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጉብኝታቸውን አጠናቀው አሰብ ገብተዋል።የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሰብ ሲደርሱ አቀባበል አድርገውላቸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰብ ወደብንና ከአሰብ ወደብ እስከ ኢትዮጵያ ድንበር ያለውን 71 ኪሎ ሜትር መንገድ የጎበኙ ሲሆን፥ መንገዱ አገልግሎት ለመስጠት በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገምግመዋል።የአሰብ ወደብን በተመለከተም ወደቡ ላይ የተወሰኑ የማስተካከያ ስራዎች ከተከናወኑ በኋላ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ወደ ስራ ይገባል ብለዋል።ዛሬ ከሰዓት በኋላም የምጽዋን ወደብ ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።የኢትዮጵያ የንግድ መርከብ ከረጅም ጊዜ በኋላ በዛሬው ዕለት ምጽዋ ወደብ ላይ መልህቋን ትጥላለች ተብሎ ነው የሚጠበቀው።(ምንጭ፤ ኤፍ ቢ ሲ)
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/30293/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
4c0f0a59b70624a243d3ace53af14b71
970fbe082a202860e9813b3ab3520ae2
“ሱዳን በሰሜን ዳግላሽ አካባቢ ድንበር ጥሳ ወደ ኢትዮጵያ መግባቷ የሁለቱን ሀገራት የቀደመ ስምምነት የጣሰ ነው” አምባሳደር ኢብራሂም እድሪስ
“ሱዳን በሰሜን ዳግላሽ አካባቢ ድንበር ጥሳ ወደ ኢትዮጵያ መግባቷ የሁለቱን ሀገራት የቀደመ ስምምነት የጣሰ ነው” አምባሳደር ኢብራሂም እድሪስባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 28/2013 ዓ.ም (አብመድ) ሱዳን በሰሜን ዳግላሽ አካባቢ ድንበር ጥሳ ወደ ኢትዮጵያ መግባቷ የሁለቱን ሀገራት የቀደመ ስምምነት የጣሰ እንደሆነ የሁለቱ ሀገራት የጋራ ድንበር ኮሚሽን አባል አምባሳደር ኢብራሂም እድሪስ ተናገሩ።የድንበር ችግሩ የሚፈታው በሀገራቱ ስምምነት እና በዓለም አቀፍ መርህ እንደሆነ የጠቀሱት አምባሳደሩ፣ በቅርቡ በድንበር አካባቢ የተፈጠረው ችግር እ.ኤ.አ በ1972 የሰሜን ዳግላሽ አካባቢ ባለበት ነባራዊ ሁኔታ እንዲቆይ የተደረሰውን ስምምነት የጣሰ ነው ብለዋል።በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ መሠረት ድንበሩን ለማካለል የሁለቱ መንግሥታት ከመፍትሔ ሐሳቦች ላይ ሲደርሱ ብቻ ነው ይላል። ይህ ማለት በአካባቢው ያለው ነባራዊ ሁኔታ በሁለቱም ሀገሮች ተከብሮ እንዲቆይ ያስገድዳል ብለዋል።በቅርቡ ኢትዮጵያ በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል ሕግ የማስከበር ሥራ ላይ እንዳለች የሱዳን ጦር በዳግላሽ ሰሜን አካባቢ ድንበር ጥሶ በመግባት ነባራዊ ሁኔታውን አደጋ ላይ መጣሉን አምባሳደር ኢብራሂም ጠቅሰዋል።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%88%b1%e1%8b%b3%e1%8a%95-%e1%89%a0%e1%88%b0%e1%88%9c%e1%8a%95-%e1%8b%b3%e1%8c%8d%e1%88%8b%e1%88%bd-%e1%8a%a0%e1%8a%ab%e1%89%a3%e1%89%a2-%e1%8b%b5%e1%8a%95%e1%89%a0%e1%88%ad-%e1%8c%a5%e1%88%b3/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
52fc7530b955d567ebef618491a7571e
292b2cfbeae964e91464448c01c6ceb3
ኮሮናቫይረስ ፡ ወገናቸውን ለመታደግ በመረጃና በጥናት የሚተጉት ዶክተር በአሜሪካ
አሜሪካ ውስጥ በዋሽንግተን ዲሲ በተላላፊ በሽታዎች ዙሪያ እየሠሩ የሚገኙት ዶ/ር ገበየሁ ተፈሪ የመጀመሪያ ከፍተኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በጎንደር የህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ነው። ሙያን ለማኅበረሰብ ትክክለኛ የጤና መረጃ የወርሽኞች ስጋት የህክምና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ጋምቤላና አዲስ አበባ ውስጥ ለጥቂት ዓመታት በሙያቸው አገልግለው ወደ አሜሪካ በማቅናት ተጨማሪ የህክምና ትምህርት በመከታተል የውስጥ ህክምና [ኢንተርናል ሜዲሲን] እና በተላላፊ በሽታዎች ተመርቀዋል።ዶ/ር ገበየሁ በአሁኑ ወቅት አሜሪካ ውስጥ የሚሠሩበት የጤና ተቋም በዋሽንግተን ዲሲ የተለያዩ የህክምና ማዕከላትን ያቀፈ ሲሆን በአካባቢው የተላላፊ በሽታ ጉዳዮችን በተመለከተ አማካሪ ሆነው እየሠሩ ይገኛሉ። ዶ/ር ገበየሁ ባሉበት የቨርጂኒያ አካባቢ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኢትዮጵያና የኤርትራ ማኅበረሰብ አባላት ከመኖራቸው አንጻር በቅርበት ከመስራታቸው በተጨማሪ በሜሪላንድ፣ በዲሲ እና ቨርጂኒያ ውስጥ ከሚገኙት እነዚህ ማኅበረሰቦች በተጨማሪ ሌሎችንም በሙያቸው እያገለገሉ ይገኛሉ። የዶ/ር ገበየሁ ተፈሪ ዋነኛ ትኩረት በኤችአይቪ፣ ሄፐታይተስ ቢ፣ ሲ እና ሌሎችም ተላላፊ በሽታዎች ላይ ሲሆን፤ የሥራ ኃላፊነታቸውም ከእነዚሁ በሽታዎች ጋር ከመያያዙ በተጨማሪ በአካባቢው ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በተላላፊ በሽታዎች ላይ በሚደረጉ ጥናቶች ዙሪያ የድርጅቱ ተወካይ በመሆን ይሠራሉ። ሥራቸውን በሚያከናውኑበት ቦታና የተለየ ትኩረት ከሚሰጧቸው በሽታዎች አንጻር ይህ አጋጣሚ "ለማኅበረሰቡ በሙያዬ ብዙ ነገር ማብርከት እንድችል አድርጎኛል" ይላሉ ዶ/ር ገበየሁ።በዚህም ከሰባት ዓመታት በፊት ማኅበረሰቡን ለማገልገል በማሰብ የእራሳቸውን ድረ ገጽ ጀመሩ። በድረ ገጻቸውም ዶ/ር ገበየሁ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያንን ሊጠቅሙ ይችላሉ የሚሏቸውን የጤና መመሪያዎችን፣ ማብራሪያዎችንና የተለያዩ መረጃዎችን ወደ አማርኛ በመተርጎም ይጋራሉ። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ ደግሞ የተለመደውን የህክምና አገልግሎት መረጃዎችን ገታ አድርገው ስለ አዲሱ በሽታ ይጠቅማሉ ብለው ያሰቧቸውን መረጃዎችን በየቀኑ እያጋሩ ይገኛሉ።ዶ/ር ገበየሁ "በተቻለኝ አቅም ሕዝቡን ለማገልገል የወሰድኩትን መሃላ ለማሳካት እጥራለሁ። ከድረ ገጹ በተጨማሪ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ላይ በመቅረብ ጠቃሚና ነፍስ አዳን ይሆናሉ ብዬ የማስባቸውን መረጃዎች አካፍላለሁ" ይላሉ።አክለውም ማኅበረሰቡ በሚረዳው በቋንቋ የሚቀርቡ መረጃዎች እጥረት ይኖራል ብለው ስላመኑ፤ እንዲሁም በተለይ በኮቪድ-19 ዙሪያ የተለያዩ የሚያሳስቱ መረጃዎች በማኅበራዊ ድረ ገጾች እየተስፋፉ በመሆናቸው ይህንን "እንደግል ግዴታዬ በመውሰድ የድርሻዬን ላበርክት ብዬ ነው የጀመርኩት" በማለት ስለሥራው አስፈላጊነት ይናገራሉ። "ኅብረተሰቡ ለእንደዚህ ዓይነቱ መረጃ አዲስ ነው" የሚሉት ዶ/ር ገበየሁ "በሚዲያ ይወራ እንጂ፣ ስል ተላላፊ በሽታዎች ሥርጭትና ጉዳት፣ ስለቫይረስ መሰረታዊ እውቀት የሌለው ሰው በሚረዳው ቋንቋ መረጃ መቅረብ አለበት ብዬ ነው እያስተማርኩ ያለሁት" ይላሉ።በዚህ ዘመን የምድራችን አሳሳቢው የጤና ጠንቅ የሆነውና አሜሪካንን ክፉኛ ያጠቃት የኮሮናቫይረስ ልክ እንደ አፍሪካ አሜሪካዊያን እና ሂስፓኒክ ዝርያ እንዳላቸው ማኅረሰቦች በዚያ ያሉ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ማኅበረሰቦችም ተጋላጭ ናቸው ይላሉ ዶ/ር ገበየሁ። እነዚህ ማኅበረሰቦች አብዛኛዎቹ የተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ፣ የሚኖሩባቸው አካባቢዎች፣ የአኗኗር ዘይቤያቸው እንዲሁም ባህላቸው ከሰዎች ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ለበሽታው ያላቸውን ተጋላጭነት ከፍ እንደሚያደርገው ያስረዳሉ። "ከዚያም በተጨማሪ ወረርሽኙ ያልታሰበ በመሆኑ ከማኅበረሰባችን አንዳንዶች ነቃ ብለው የሚያስፈልገውን እርምጃ ቢወስዱ እንኳን ብዙዎች ግን ከመረጃ ማጣትና ከመዘናጋት የተነሳ ተጠቂ የሆኑ ነው" በማለት አመልክተው ይህንን የመረጃ ክፈተት ለመሙላት በሙያቸው እየጣሩ እንደሆነ ዶ/ር ገበየሁ ይናገራሉ። ማኅበረሰቦቹ በተለይ ለወረርሽኙ ተጋላጭ የሚሆኑት ከባህላቸውና ከአኗኗራቸው የተነሳ "በስፋት መገናኘታቸው፣ በመደበኛነት መጠያየቃቸው እና በሌሎች የተለያዩ ምክንያቶች ለቫይረሱ በመጋለጣቸው በቫይረሱ የመዛመትና የመሠራጨት ጉልበት የተነሳ ብዙዎችን ጉዳት ላይ ጥላሏል" በማለት ትኩረት የሚሻውን የበሽታው መተላለፊያ መንገድን ትኩረት ይሰጡታል። ዶክተር ገበየሁ በተለይ በበሽታው ተጠቂ የሆኑት የማኅበረሰቡ ክፍሎት ሰፋ ያለ የቤተሰብ አባላት ያላቸው እንደነበሩ አመልከተዋል። በሽታውበዓለም ዙሪያ በርካቶችን እየያዘ በሺህዎች የሚቆጠሩትን ለሞት እየዳረገ ሲሄድ በአሜሪካ ሚሊዮኖች በቫይረሱ መያዘቸው እንዲሁም ከ200 ሺህ በላይ የሚሆኑት በበሽታው ሰበብ ሞተዋል። በሽታውን ለማወቅና እራስን ለመጠበቅ ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ጠቃሚ እንደሆነ የሚናገሩት ዶ/ር ገበየሁ እንደሚሉት የተለያዩ ወገኖች እርስበርስ የሚጣረሱና አሳሳች መረጃዎችን በማኅበራዊ ሚዲያዎች በኩል በቀላሉ ስለሚያሰራጩ የሚታመኑ የመረጃ ምንጮችን መጠቀምን ይመክራሉ።ለዚህም መፍትሄው "እንደ ዓለም ጤና ድርጅትና በየአገሩ ያሉ ተመሳሳይ ተቋማትን ምክር መከተሉ ተመራጭ ነው" የሚሉት ዶ/ር ገበየሁ፤ የሚወጡ መረጃዎችን በተመለከተም በመረዳትና ተግባራዊ በማድረጉ በኩል ልዩነቶች እንዳሉ ይናገራሉ።ከመረጃዎች አንጻር "በህክምናው ዘርፍ በተሰማሩ ሰዎች መካከል ልዩነት አለ። ሥራችን በተላላፊ በሽታዎች ላይ ያተኮርንና በሌላ ዘርፍ የተሰማሩ ሐኪሞች እንኳን ነገሮችን የመረዳት ሁኔታው የተለያ ሊሆን ይችላል። ለዚህ ነው ማኅበረሰቡ የሚያገኘው መረጃ በሚገባው ቋንቋና ከመሆኑ በተጨማሪ ትክክለኛ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል" ይላሉ። ስለዚህም ዶ/ር ገበየሁ እንደሚሉት ዋና ነገር መሆን ያለበት "ለማኅበረሰቡ የሚደርሰው መረጃ በሙያው ላይ በተሰማሩ ሐኪሞች መሆን አለበት" ባይ ናቸው። "በተላላፊ በሽታ የተጠቁ ህሙማን የሚከታተሏቸውን ወይም የሚያክሟቸውን ባለሙያዎች ምክርን መከተል በሽታውን ለመካላከልና ከበሽታው ለመዳን ትልቅ አስተዋጽዖ አለው" ይላሉ።"ኮቪድ-19 ስም እና በሽታው አዲስ ይምሰል እንጂ በየተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥር ዘርፍ የቆየ ቫይረስ ነው" የሚሉት ዶ/ር ገበየሁ፤ ከኤችአይቪ አንስቶ የተለያዩ በሽታዎችን እያጠኑ ላሉ እሳቸውን ለመሰሉ ባለሙያዎች አዲስ አይደለም። ተላላፊ በሽታዎች ላይ የተለየ ትኩረት አድረገው የሚሰሩት ዶ/ር ገበየሁ በሽታ አምጪ የሆኑ ቫይረሶች ባህሪያቸው አንዱ ከአንዱ ሊለያይ እንደሚችል ይናገራሉ። በዚህ ዘርፍም የተላላፊ በሽታዎችን ባህሪያትን ለማወቅ እና ለማዳን የሚረዱት ጥናቶች በሰዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በአካባቢው ባሉ እንስሳት ላይ ጭምር እንደሆነ ይናገራሉ። "ኮሮናቫይረሶች ከሰው ጋር አብረው የኖሩ ናቸው። በአጠቃላይ ወደ አራት የሚደርሱ አሉ። ከጥንት ጀምሮ ሰው ላይ ተራ ጉንፋንና የመሳሰሉ የጤና ዕክሎችን የሚያስከትሉ ናቸው። እነርሱም ገዳይ አይደሉም" ይላሉ።ይሁንና ኮሮናቫይረስም [ኮቪድ-19] ምንም እንኳን በርካቶችን ለሞት ቢዳርግም ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው የሚናገሩት ዶ/ር ገበየሁ "በጣም ገዳይ የሆነ ቫይረስ ሰዎችን ገድሎ አብሮ ይከስማል" በማለት ሞትን በሚያስከትሉ ቫእረሶች መካከል ያለውን ልዩነት ያስረዳሉ።ጨምረውም አደገኛ ወይም ገዳይ የሚባል ቫይረስ አብዛኛውን ጊዜ የሚይዘውንና የሚገድለውን ገድሎ አብሮ የሚሞት መሆኑን አመልክተው፤ ለእንዲህ አይነት ቫይረሶች ክትባትና መድኃኒት ለማግኘት ፈታኝ ነው ይላሉ።እንደምሳሌም ሳርስ ቁጥር አንድ የተሰኘው ቫይረስ የሚጠቅሱት ዶ/ር ገበየሁ፤ ይህ በሽታ ተከስቶ ጉዳት አድርሶ በመክሰሙ ክትባት ቢዘጋጅም በሽታው እንደጠፋ የቀረ። የተላላፊ በሽታዎችን በሚያጠኑና በሚያክሙ ባለሙያዎች ዘንድ አሳሳቢውና አስፈሪው ነገር "እየደጋጋሙ የሚመላለሱ ወረርሽኞች ናቸው" ይላሉ፤ ምክንያቱንም ሲያስቀምጡ እንዲህ አይነት ወረርሽኞች ባህሪያቸው የሚጨበጥ አለመሆኑን ይናገራሉ። በተለያዩ ቫይረሶች መካከል የሚፈጠር መዛመድም አደገኛ ውጤትን ሊያስከትል እንደሚችል የሚናገሩት ዶ/ር ገበየሁ "በሙያችን 'ቫይረስ ሴክስ' የሚባል ነገር አለ። ሁለት ቫይረሶች እርስ በእርስ 'ጄኔቲክ ኮድ' [የዘረመል አወቃቀር ይዘት] በመቀያየር አዲስ ቫይረስ ይፈጥራሉ ወይም ልጅ ይወልዳሉ እንላለን።" ለምሳሌ ይህ ኮቪድ-19 ከሜርስ ጋር ቢገናኝና ዘረመል ቢለዋወጡ አደገኛ ውጤትን ሊያስከትሉ ይችላሉ፤ ምክንያቱም ሜርስ ገዳይ ነው የጎደለው ከሰው ወደ ሰው መተላለፍ ብቻ ነው። ኮቪድ-19 ደግሞ ነባርና አደገኛ የጤና እክል ያለው ሰው ካልሆነ በስተቀር የመግደል አቅሙ ደካማ ነው። ሆኖም ግን ከሰው ሰው የመተላለፍ አቅሙ በጣም ፈጣን ነው። "ለዚህም ነው ሁለቱ ቢገናኙና የባህሪይ መወራረስ ቢፈጠር በጣም አደገኛ ቫይረስ ሊወልዱ/ሊፈጥሩ ይችላሉ" ብለው ዶ/ር ገበየሁ በቫይረሶች መካከል የሚኖር መዛመድ አንደኛው ከሌላኛው አደገኛ ባህሪዎችን በመውሰድ አደገኛ ውጤትን ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ያስረዳሉ። ዶክተር ገበየሁ እንደሚሉት ለሰው ልጆች ጤና ጠንቅ የሆኑ ቫይረሶች በአንድ ስያሜ የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ። "ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው ኤችአይቪ ነው" የሚሉት ዶክተሩ፤ "ብዙ ሰው አንድ ዓይነት ኤችአይቪ ያለ ይመስለዋል" ይላሉ። ነገር ግን "ሁለት አይነት የኤችአይቪ ዓይነቶች ያሉ ሲሆን፤ አንደኛው በአራት የሚከፈል ሲሆን ከእነርሱ መካከል ደግሞ አንደኛው 14 ዝርያዎች ያሉት የቫይርስ ዓይነት ነው" በማለት ከዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላ እንኳን መድኃኒት ማግኘት አስቸጋሪ የሆነው በዚህ የቫይረሶቹ አይነት መብዛት እንሆነ ያመለክታሉ። ሲያጠቃልሉም በዚህ ዘመን የተከሰተውን ወረርሽኝን በተመለከተ በሽታው እየቀነሰ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን እየተስፋፋ መሆኑ ብዙ ሰዎች ላይ ፍርሃትን እንደሚፈጥር የሚጠቅሱት ዶ/ር ገበየሁ፤ በዚህም ሳቢያ በሰዎች ዘንድ የተፈጠረውን ፍርሃት በመጠቀም ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎች ሊስፋፉ ስለሚችሉ የመጠንቀቅን አስፈላጊነት ያሰምሩበታል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.bbc.com/amharic/news-54252616
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
0bf31f0d2f70297064774cd114192a7e
95b9a7854debef8d9c43a638e6690686
የባንኮች ማኀበር ፕሬዚዳንቱንና ምክትሉን መረጠ
ሁሉንም የግልና የመንግሥት ባንኮች በአባልነት የያዘው የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር፣ የደቡብ ግሎባል ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አዲሱ ሃባን ለቀጣዮቹ ሦስት ዓመት በፕሬዚዳንትነት እንዲያገለግሉት መረጣቸው፡፡ማኅበሩ በቅርቡ ባደረገው ምርጫ በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲያገለግሉ የተመረጡት ደግሞ፣ የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ናቸው፡፡ ከአቶ አቤ ቀደም ብሎ ማኅበሩ በምክትል ፕሬዚዳንትነት ሲያገለግሉ የቆዩት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ በቃሉ ዘለቀ ነበሩ፡፡ የማኅበሩ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት የተመረጡት፣ በዕጩነት የቀረቡ ተመራጮች ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ መሠረት ነው፡፡ በማኅበሩ ደንብ መሠረት ከፍተኛ ድምፅ ያገኘው ፕሬዚዳንት፣ ሁለተኛውን ከፍተኛ ድምፅ ያገኘው ደግሞ ምክትል ፕሬዚዳንት ይሆናሉ፡፡ ከዚህ የፕሬዚዳንትና የምክትል ፕሬዚዳንትነት ምርጫ ቀደም ብሎ ማኅበሩ ለ12 የቦርድ አባላት ምርጫ ማካሄዱን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአዲሱ የቦርድ አባላት ምርጫ የተመረጡት የኢትየጵያ ንግድ ባንክ፣ የአዋሽ ባንክ፣ የዳሸን ባንክ፣ የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ የኅብረት ባንክ፣ የንብ ባንክ፣ የደቡብ ግሎባል ባንክ፣ የዘመን ባንክ፣ የብርሃን ባንክ፣ የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ የአዲስ ኢንተርናሽናል ባንክና የአቢሲኒያ ባንክ ፕሬዚዳንቶች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር በ1994 ዓ.ም. ሲቋቋም የመጀመርያው የማኅበሩ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉት፣ በወቅቱ የአዋሽ ባንክ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ላይከን ብርሃኑ ናቸው፡፡ ከእሳቸው ቀጥሎ የፕሬዚዳንትነቱን ቦታ የተረከቡት ደግሞ የአሁኑ የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አዲሱ ሃባ ነበሩ፡፡ አቶ አዲሱ ሁለተኛው የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት የኮንስትራክሽን ቢዝነስ ባንክ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ነው፡፡ ከአቶ አዲሱ ቀጥሎ የማኅበሩ ሦስተኛው ፕሬዚዳንት የኅብረት ባንክ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ብርሃኑ ጌታነህ ናቸው፡፡ አቶ ብርሃኑ የኃላፊነት ዘመናቸው ሳያጠናቅቁ በፈቃዳቸው በመልቀቃቸው በእርሳቸው ምትክ አቶ አዲሱ ሃባ ቦታውን እንዲይዙ ተደርጎ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ በሰሞኑ የማኅበሩ ምርጫ አቶ አዲሱ በድጋሚ መመረጣቸው በሦስት የተለዩ ባንኮች ፕሬዚዳንትነት ለሦስት የምርጫ ዘመኖች ማኅበሩን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት የመጀመርያው ያደርጋቸዋል፡፡ አቶ አዲሱ በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ከ40 ዓመታት በላይ ያገለገሉ ሲሆን፣ በ1969 ዓ.ም. የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ በሚባል ይታወቅ የነበረውንና አሁን ከንግድ ባንክ ጋር የተቀላቀለውን ከክለርክት እስከ ፕሬዚዳንትነት አገልግለዋል፡፡ የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክን ከለቀቁ በኋላ የአቢሲኒያ ባንክ ፕሬዚዳንት ሆነው ሠርተዋል፡፡ ከአቢሲኒያ ባንክ በኋላ ደግሞ በአሁኑ ወቅት የደቡብ ግሎባል ባንክ ፕሬዚዳንት በመሆን በማገልገል ላይ ናቸው፡፡  የማኅበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ የተመረጡት አቶ አቤ ሳኖ ደግሞ በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ወደ 20 ዓመታት ሠርተዋል፡፡ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋም ከወጡ በኋላ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የተቀላቀሉት አቶ አቤ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ በወጣትነታቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት መሆን የቻሉ ናቸው፡፡ አቶ አቤ ባልተለመደ ሁኔታ የኢትየጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት ሆነው ሲሾሙ በወቅቱ የ31 ዓመት ወጣት ነበሩ፡፡ ፕሬዚዳንት ከመሆናቸው ቀደም ብሎ ባንኩ ውስጥ ለአጭር ጊዜ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ ሲሆን፣ ንግድ ባንክን ከለቀቁ በኋላ ደግሞ ከምሥረታው ጀምሮ የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዚዳንት በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር ዋነኛ ዓላማው አድርጎ ያስቀመጠው በባንኮች መካከል የእርስ በርስ ግንኙነት ማዳበርና መረጃ እንዲለዋወጡ ማድረግ የሚለው ይገኝበታል፡፡ በጋራ በሚከናወኑ ሥራዎች ላይ ተባብሮ ለመሥራት አመቺ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ሌላው ዓላማው ነው፡፡ የባንክ ዘርፉን ለማስፋፋት ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን መሥራት፣ በባንክ ኢንዱስትሪው ላይ ጥናት ማካሄድ፣ ባንክን የሚመለከቱ የሚወጡ መመርያዎችና ደንቦችን በማስጠናት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር አመቺ ሁኔታዎች እንዲኖሩ ማስቻልና የባንክ ባለሙያዎች ማሠልኛ ተቋማትን የመገንባት ዕቅድ አለው፡፡
ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/article/8317
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
67f13b386150ebac025d75584561b0df
71d6879ef492f1d50d69a82e3a63e52a
የመሬት ሊዝ ጨረታ በግርግር ታጅቦ ተከፈተ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ራሱ ባበለፀገው አዲስ ሶፍትዌር ታግዞ ይፋ ያደረገው 29ኛው የመሬት ሊዝ ጨረታ በግርግር ታጅቦ ተከፈተ፡፡ ጨረታው ለአንድ ካሬ ሜትር መሬት ዝቅተኛው 12 ሺሕ ብር ከፍተኛው 100 ሺሕ ብር የመወዳደሪያ ዋጋ ቀርቧል፡፡       የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ተግባራዊ ያደረገው አዲስ ሶፍትዌር፣ ካሁን በፊት ተግባራዊ ሲሆን የቆየውን የሊዝ ጨረታ ሒደት የቀየረ በመሆኑ፣ ጨረታው በተከፈተበት ወቅት ከፍተኛ ግርግርና መተራመስ ተፈጥሯል፡፡      በሰባቱ ክፍላተ ከተሞች ለጨረታው የቀረቡትን 100 ቦታዎች ለማግኘት የሚወዳደሩ ተጫራቾች የመጨረሻውን ቀን ሳይጠብቁ  መረጃቸውን ቀድመው ቢሮው ባዘጋጀው ኮምፒዩተር ላይ መጫን ይጠበቅባቸው ነበር፡፡      ነገር ግን በርካታ ተጫራቾች ሰነዳቸውን በመጨረሻው ቀን ይዘው በመቅረባቸው ከፍተኛ ሠልፍ፣ ግርግርና መተራመስ ተፈጥሯል፡፡ ከዚህ ባለፈም ተራቸው ሳይደርስ ወደ ውስጥ ለመግባት የሞከሩ ተጫራቾች እርስ በእርስ እንዲሁም ከፖሊስ ጋር ተጋጭተዋል፡፡      በመጨረሻ ሰዓት ሰነድ ገዝተው ሲፒኦ አሠርተው የቀረቡ መሬት ፈላጊዎች በጨረታው ሳይወዳደሩ ቀርተዋል፡፡      ለጨረታ የቀረቡት 100 ቦታዎች ከመቶ ካሬ ሜትር እስከ 1‚244 ካሬ ሜትር ድረስ ስፋት አላቸው፡፡ ለጨረታ የቀረቡት ቦታዎች የሚውሉትም ለቢዝነስ፣ ለመኖሪያና ለቅይጥ አገልግሎቶች ነው፡፡      የከንቲባ ድሪባ ኩማ አስተዳደር በሥልጣን ዘመኑ መጨረሻ ዓመት ላይ 29ኛውን የሊዝ ጨረታ ግንቦት 27 ቀን 2010 ዓ.ም. አውጥቷል፡፡ ተጫራቾች ያቀረቡት ሰነድ አዲስ በተዘጋጀው ሶፍትዌር ሲሞላ ቆይቶ፣ ማክሰኞ ሰኔ 12 ቀን 2010 ዓ.ም. ተከፍቷል፡፡      በወቅቱ ለአንድ ቦታ የተወዳደሩ በሰጡት ዋጋ መሠረት ከአንድ እስከ ሦስት ድረስ የወጡ ተወዳዳሪዎች ይፋ ተደርገዋል፡፡ ይህ አዲስ አሠራር ከዚህ በፊት የነበሩ ብልሹ አሠራሮችን፣ ጣልቃ ገብነቶችንና ከተጫራቾች ይነሱ የነበሩ ቅሬታዎችን ይፈታል ተብሏል፡፡      የመሬት ፈላጊዎች ቁጥር በየጊዜው እያደገ ቢመጣም፣ የከተማ አስተዳደሩ ግን መሬት ለጨረታ የሚያቀርብበት ጊዜም ሆነ ቁጥር እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ የአሁኑ ጨረታ እንኳ ከዘጠኝ ወራት ቆይታ በኃላ የወጣ ነው፡፡ የመሬት ሥሪት ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ መሬት በብዛትና በፍጥነት እስካልቀረበ ድረስ የመጫረቻ ዋጋው እየጨመረ ይሄዳል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/article/11505
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
03974faeff57e24c0eddfb8e76b7137b
4155951a631b912547f40a6af6db2c17
ንጉሥ ካሌብ ጻድቅ
ስመ ንግሡ ዳግማዊ ዐፄ እለ አጽብሃ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተብሎ የተሰየመ ይህ የከበረ ጻድቅ የኢትዮጵያ ንጉሥ ካሌብ እግዚአብሔርን የሚፈራውና በፍጹም ልቡ የሚወደው ሃይማኖቱም የቀና ሰው ነበረ ። ሥጋዊና መንፈሳወዊው ተጋድሎ ክፍል ፩ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት አምስት መቶ ሃያ ዐራት ዓመት በኋላ በናግራን ሀገር በክርስቲያኖች በአይሁዶችና በአረማውያን መካከል ከባድ ፀብ ተነሣ ። በዚህን ጊዜ ማዝሩቅ ወይም ፊንሐስ የተባለው የሂማሪያው ንጉሥ የአረመኔዎቹንና የአይሁዶቹን ምክር እየተቀበለ ክርስቲያኖቹን ፈጃቸው ። አብያተ ክርስቲያናቱንም ሁሉ አቃጠለ ። ከዚህ ሁሉ በፊት የከሓዲው ንጉሥ ክርስቲያኖቹን የናግራንን ሰዎች ፤ ክርስቶስን ብትክዱት ሕይወታችሁ ይጠበቃል ። ማንኛውም መከራና ሥቃይ ወይም ጥፋት ሊያገኛችሁ አይችልም አለቸው ። እነዚህ ቅዱሳን ሰማዕታት ግን በአምላክነቱ አምነን በስሙ የተጠመቅን እኛስ ክርስቶስን ልንክደው አንችልም ሲሉ በታላቅ ቃል ጮሁ። ዳግመኛም ይህ አላዊ ንጉሥ አምላካችን የምትሉት ክርስቶስ ከእጄ የሚያድናችሁ ይመስላችኋልን? ከዚህ ከሚያስፈራና ከሚያስደነግጥ ሥቃይና መከራ ሊያወጣችሁ ይቻለዋልን? ወደዚህስ ቀርቦ ከእኔ ጋር ይዋጋ ዘንድ ይቻለዋልን አላቸው ።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
e30d253dd8f5bb94e3e7d9c7deb295d3
172e10979a14a20e1372772604b3dd25
ጠ/ሚ ዐቢይ በመስኖ ልማት የስንዴ ምርታማነትን ለመጨመር መታቀዱን አስታወቁ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስንዴን ከውጭ በማስገባት ፈንታ በመስኖ በማልማት ምርታማነት ለመጨመር መታቀዱን አስታወቁ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስ ቡክ ገጻቸው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛውን የስንዴ መጠን ለማምረት ከሚችሉ ሀገራት መካከል መሆኗን አስታውቀዋል።የስንዴ ምርት አሁን ከውጭ ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በጋምቤላ በቅርቡ ተስፋ የሚጣልባቸው ውጤቶች መታየታቸውን አንስተዋል።ከዚህ ባለፈም በሶማሌ ክልል ያለው የቆላ ስንዴ ምርት የሚያበረታታ መሆኑንም ጠቁመዋል።አያይዘውም ለዓመታዊው የአረንጓዴ ዐሻራ የሚሆን ችግኝ በሦስቱም ክልሎች በሚገባ እየተዘጋጀ መሆኑን መገንዘባቸውንም አውስተዋል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8c%a0-%e1%88%9a-%e1%8b%90%e1%89%a2%e1%8b%ad-%e1%89%a0%e1%88%98%e1%88%b5%e1%8a%96-%e1%88%8d%e1%88%9b%e1%89%b5-%e1%8b%a8%e1%88%b5%e1%8a%95%e1%8b%b4-%e1%88%9d%e1%88%ad%e1%89%b3%e1%88%9b%e1%8a%90/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
71f66c97300642e423fc8b59f21e357a
eb23421b6405fed4d416f383ed403f54
የዩጋንዳ መንግሥት ለደቡብ ሱዳን መንግሥት የጦር መሣሪዎችን ሲያደርስ መቆየቱ ይፋ ተደረገ
የዩጋንዳ መንግስት አለምዓቀፉን የጦር መሳሪያዎች እገዳ በመጣስ ለደቡብ ሱዳን መንግስት የጦር መሳሪያዎችን ሲያደርስ መቆየቱን አንድ ጥናት ይፋ አድርጓል፡፡አንድ መቶ አምስት ገጾች ያሉት የጥናት ሪፖርቱ ለደቡብ ሱዳን የተሸጡ መሳሪያዎችንና ጥይቶችን የሚያሳይ ማስረጃ መያዙም ተነግሯል፡፡ በደቡብ ሱዳን ላይ ለረጅም ጊዜ ያስቆጠረ የጦር መሳሪያዎች ማዕቀብ ቢጣልም አሁንም ድረስ አዳዲስ የጦር መሳሪያዎች በጎረቤት ሀገራት በኩል በእርሰ በእርስ ግጭት ለቆየችው ደቡብ ሱዳን የጦርነት ቀጠናዎች ሲደርሱ መቆየታቸው ይነገራል፡፡አራት አመታትን የፈጀውና መቀመጫውን እንግሊዝ ለንደን ባደረገው ለግጭቶች መንስኤ በሚሆኑ የጦር መሣሪያዎች ላይ ጥናት በሚያደርገው ተቋም ይፋ የሆነው መረጃ በተለይም በጎረቤት ሀገር ዩጋንዳ በኩል እየገባ ያለው የጦር መሳሪያ እንደአውሮፓውያኑ የዘመን ቀመር በ2013 የጀመረው የደቡብ ሱዳን የእርስ በእርስ ግጭት እንዲባባስ ምክንያት ሆኖ መቆየቱን አመልክቷል፡፡የዩጋንዳ መንግስትም አለማቀፉን የጦር መሳሪያዎች እገዳ በመጣስ ለደቡብ ሱዳን መንግስት የጦር መሳሪያዎችን ሲያደርስ መቆየቱንም ነው ጥናቱ ይፋ ያደረገው፡፡አንድ መቶ አምስት ገጾች ያሉት ይኸው የጥናት ሪፖርት ለደቡብ ሱዳን የተሸጡ መሣሪያዎችንና ጥይቶችን የሚያሳይ ማስረጃ አያይዟል፡፡የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት እንደአውሮፓውያኑ የዘመን ቀመር ሀምሌ 2018 በደቡብ ሱዳን ላይ የጦር መሳሪያ ማዕቀብ ከማስተላለፉ በፊት የአውሮፓ ህብረት በአባል ሀገራቱ በኩል ለሱዳን የሚከናወን ማንኛውንም አይነት የጦር መሳሪያ ሽያጭ እ.ኤ.አ ከ1994 ጀምሮ አግዶ ነበር፡፡ይህ ማዕቀብም እ.አ.ኤ በ2011 ከሱዳን በመገንጠል ነጻነቷን የተቀዳጀችውን ደቡብ ሱዳንን እንዲያካትት ውሳኔ ማስተላለፉ አይዘነጋም፡፡ይሁን እንጂ ለሱዳን መንግስት ጦር አልፎ አልፎ ከአሜሪካና ከአውሮፓ ሀገራት የሚመጡ የጦር መሳሪያዎችን በዩጋንዳ በኩል ሲቀርብለት መቆየቱን ነው ጥናቱ ያመላከተው፡፡ጥናቱ በዩጋንዳ በኩል ለደቡብ ሱዳን የጦር መሳሪያ ሲያቀርቡ የነበሩት የአውሮፓ ሀገራት ስሎቫኪያ ሮማኒያ እና ቡልጋሪያ ስለመሆናቸው ጥናቱ ያስቀምጣል፡፡የተቃዋሚ ኃይሉ ግን የጦር መሣሪያዎችን በቀላሉ ማግኘት አለመቻሉን እና የወዳደቁ የጦር መሳሪያዎች ላይ ጥገኛ ለመሆን መገደዱንም ያሳያል፡፡የደቡብ ሱዳን የኢንፎርሜሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ሚካኤል ማኩዬ የጥናቱ ውጤት ትክክል አለመሆኑንና መንግስታቸው እንደማይቀበለው ለአሶሼትድ ፕሬስ ገልጸዋል፡፡በጊዜው ደቡብ ሱዳን የጦር መሳሪያ ለመግዛት ገንዘብ የላትም ነበር ያሉት ሚኒስትሩ ጁባ ደግሞ የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ለማረጋገጥ ገንዘብ ትፈልጋለች ብለዋል፡፡ በያዝነው ወር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ይፋ ያደረገው መረጃም ዩጋንዳ የጦር መሳሪያ እገዳውን በመተላለፍ ለደቡብ ሱዳን የጦር መሳሪያዎች ታቀርባለች በሚል መክሰሱ አይዘነጋም ሲል የዘገበው ዘ ገልፍ ቱደይ ነው፡፡
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/33223/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c5bc1c96945d3d9a23fafa03734a8ad5
6d41f7ec15365391a106e3ff6d09069a
የዶናልድ ትራምፕ ጋዜጣዊ መግለጫ ራሱን የቻለ የኮሜዲ ትዕይንት መልክ የሚይዝበት ጊዜ ብዙ ነው። የትናንት ምሽቱ ከነዚህ የሚመደብ ነው፡፡ በዋሺንግተን ሰኞ ከሰዓት ነው የተደረገው፤ በኛ ሌሊቱን።
ኮሮናቫይረስ፡ "ቀጣፊ ዋሾ ነሽ፣ አሳፋሪ ሰው ነሽ" ዶናልድ ትራምፕን ያስቆጣችው ጋዜጠኛ\nበትራምፕ ጋዜጣዊ መግለጫ ታሪክ ዘለግ ያለ ሰዓት ወስዷል የተባለት ይህ ጋዜጣዊ መግለጫ በድራማዎች የተሞላ ነበር። በድምሩ 2 ሰዓት ከ 24 ደቂቃ የወሰደ መሆኑም ልዩ ያደርገዋል። ወትሮም ትራምፕ ጠላቶቼ ከሚሏቸው ጋዜጠኞች ጋር የሚያደርጉት ቆይታ አንዳች አስቂኝ ክስተት አያጣውም። ለምሳሌ ባፈለው አርብ በፈረንጆች ስቅለት ዕለት በነበራቸው መግለጫ ጋዜጠኞቹን፣ "እስኪ ዛሬ እንኳ እርስ በርስ እንተሳሰብ፤ ስቅለት ነው፤ እስኪ ዛሬ እንኳ ጨዋ ሁኑ…" ብለው ነበር መድረኩን ለጥያቄ የከፈቱት። ዶናልድ ትራምፕ "ተራ ጉንፋን ነው፤ በራሱ ጊዜ ብን ብሎ እንደ ተአምር ይጠፋል" ሲሉት የነበረው ቫይረስ 600ሺህ የሚጠጋ ዜጋቸውን አጥቅቷል። ከ20ሺ በላይ አሜሪካዊያንን ገድሏል። አሁንም ቢሆን ግን እርሳቸው ስለ ስኬታቸው እንጂ ሌላ ማውራት አይወዱም። ከሰሞኑ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ዶናልድ ትራምፕ ፈጣን እርምጃ እንዲወስዱ በቂ መረጃ ቀርቦላቸው እንደነበር፣ በቂ ምክር ተሰጥቷቸው እርሳቸው በመዘናጋታቸው ነው ይህ ሁሉ ጥፋት የደረሰው የሚል ይዘት ያለው ሰፊ ዘገባ ይዞ መውጣቱ ፕሬዝዳንቱን ክፉኛ ሳይረብሻቸው አልቀረም። ለዚህም ይመስላል ሰፊ ጊዜ ወስደው በጊዜ ሰንጠረዥ ሳይቀር መቼ ምን እንዳደረጉ እስኪሰለች ድረስ ደጋግመው ሲናገሩ የነበረው። በትናንቱ የጋዜጣዊ መግለጫ መድረክ ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣን በቻሉት አቅም ሁሉ ወርፈውታል። "ቀጣፊ!" ብለውታል። • ኮሮናቫይረስ ለምን ከ50 ዓመት በላይ የሆኑ ወንዶችን ያጠቃል? ወረርሽኙን በመከላከሉ ሂደት ስማቸው ገዝፎ የሚነሳው ዶ/ር ፋውቺን ከሥራ ሊያባሯቸው ይችላሉ የሚለው ዜና ከወጣ በኋላ በተደረገው በዚህ ዘለግ ያለ የጋዜጠኞችና የትራምፕ ጥያቄና መልስ ክፍለ ጊዜ ጎልቶ የወጣው ታዲያ የፓውላ ሬይድና የትራምፕ ፍጥጫ ነው። ፓውላ ሬይድ የሲቢኤስ ጋዜጠኛ ናት። ትናንት ዶናልድ ትራምፕን በጥያቄ ተናንቃቸው ነበር። እርሷን ለመስደብ ያደረሳቸውም ፈታኝ ጥያቄዎቿን ያለማቋረጥ በመሰንዘሯ ነው። በቂ ሥራ ከጃንዋሪ ወር ጀምሮ ሠርቻለሁ ልወቀስ አይገባም የሚሉትን ትራምፕን በፌብሪዋሪ ወር ምን ሲሰሩ ነበር? በር ለመዝጋት ለምን ዘገዩ? ስትል ጠይቃቸዋለች። ትራምፕ ነገሩን ቸል ብለው ስለስኬታቸው ማውራት ሲጀምሩ እያቋረጠች ፋታ ነሳቻቸው። ይህ የሁለቱ ምልልስ የሚሊዮኖችን ቀልብ ስቧል። በግርድፉ ይህን ይመስላል። ትራምፕ፡- "በጃንዋሪ 11 አንድም ታማሚ በአሜሪካ አልነበረም። ይሄ የናንተ ዋሾ ሚዲያ ዝም ብሎ ይቀባጥራል። 'ኦ… ፕሬዝዳንቱ ቀደም ብሎ ነገሮችን መቆጣጠር ነበረበት' ይላል። ልንገራችሁ አይደል? እኔ መጀመርያ ነው እርምጃ የወሰድኩት። እርምጃ ፈጥኜ ስወስድ ደግሞ ይቺ ናንሲ ፒሎሲ የምትባል ሴትዮ እና ይሄ እንቅልፋሙ ጆ ባይደን ደርሰው ይተቹኛል። "…እንዲያውም በአየር መንገዶች ቁጥጥር እንዲደረግ በማድረጌ መጤ ጠል ሲሉኝ ነበር። በጃንዋሪ 21 ነው የመጀመርያው የቫይረሱ ተጠቂ የተገኘው። አንድ ሰው እንኳ አልሞተም። በዚህ ጊዜ ለምን የዓለሙን ትልቁን ኢኮኖሚ አልዘጋህም ነው የምትሉኝ? ምን ነክቷችኋል እናንተ ሰዎች? "…የዓለምን ቁጥር አንድ ኢኮኖሚ፣ ቻይናን የሚያስከነዳውን ኢኮኖሚ፣ የታላቋን አሜሪካንን ኢኮኖሚ፣ ታላቁን ቀጣሪ ኢኮኖሚ…በዚያ ወቅት ለምን አልዘጋህም ነው የምትይኝ? ደግሞ ትልቅ ኢኮኖሚ የገነባሁት እኔ ነኝ። በጃንዋሪ 31 በዚች ታላቅ አገር አንድ ሰው ሳይሞት ነው በር የዘጋሁት። • ቻይና ከኮሮናቫይረስ ጋር ያደረገችውን ፍልሚያ በቅርብ የታዘበው ኢትዮጵያዊ ዶክተር "…ቶሎ በር ስዘጋ ደግሞ እናንተ ሐሳዊ መረጃ ፈልፋዮች የትችት መዓት ታደርሱብኛላችሁ፤ የሚገርም እኮ ነው፤ ስፈቅድም መከራ፣ ስከለክልም መከራ… "…እንቅልፋሙ ጆ...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
591e261e3966a58e53642b600b92f158
263bbef2924c431c2946f9a1f4abc677
ዜና እረፍት |የቀድሞው የሻሸመኔ ከተማ አሰልጣኝ በድንገተኛ የመኪና አደጋ ህይወታቸው አለፈ
ሻሸመኔ ከተማን ከምስረታው ጀምሮ ለረጅም ጊዜያት ያሰለጠኑት አሰልጣኝ ደጀኔ ጫካ ትላንት ምሽት በድንገተኛ አደጋ ህይወታቸው አለፈ፡፡በሻሸመኔ ስፖርት ክለብ ታሪክ ውስጥ ስማቸው ጎልቶ ከሚጠሩ እና በርካታ ታዳጊዎች ማፍራት ከቻሉ አሰልጣኞች መካከል የነበሩት አሰልጣኝ ደጀኔ ከ1970ዎቹ ጀምሮ በአካባቢው በሚገኙ ቡድኖች እና ለወረዳ እንዲሁም ለሀዋሳ ዱቄት ክለብ በተጫዋችነት ያሳለፉ ሲሆን ወደ አሰልጣኝነቱ ከመጡ በኃላ ትልቅ ስራዎች ሰርተው አልፈዋል። ሻሸመኔ ከተማን በ1990 መባቻ ጀምሮ መሠረት እንዲይዝ ያደረጉ ሲሆን ሻሸመኔ ከተማን ከኦሮሚያ ሊግ አንስቶ በብሔራዊ ሊግ እንዲሁም በ1999 ወደ ፕሪምየር ሊግ በማሳደግ ሁለት የውድድር ዘመናትን በሊጉ ማሳለፍ ችለው የነበረ ሲሆን እስከ 2004 መጨረሻ ድረስም ቡድኑን በአሰልጣኝነት መርተውታል።ባለፉት አመታት ከእግርኳሱ ርቀው በንግድ ስራ ተሰማርተው ኑሯቸውን እየገፉ የነበሩት አሰልጣኝ ደጀኔ ጫካ ትላንት በሚኖሩባት ሻሸመኔ ምሸት 5:00 ላይ በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ምክንያት በተወለዱ 50 አመታቸው ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል። ባለትዳር እና የ3 ልጆች አባት የነበሩት አሰልጣኝ ደጀኔ ነገ ረፋድ በሻሸመኔ ቅዱስ ዮሀንስ ቤተክርስቲያን ስርአተ ቀብራቸው የሚፈፀም ይሆናል፡፡ሶከር ኢትዮጵያ በአሰልጣኝ ደጀኔ ጫካ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማትን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀች ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጅ ዘመድ እና ለስፖርት ቤተሰቡ መፅናናትን እንመኛለን!
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/36963
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
6a58019b6a988d96c256a97010a5cd13
9107b44f18904188174095cc9cc022d4
ዩኒቨርሲቲዎች ከአለም አቀፍ ተቋማት ጋር ትስስራቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል – ምሁራን
በኢትዮጵያ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከአለም አቀፍ ተቋማት እና ምሁራን ጋር ያላቸዉ ትስስር እንዲያጠናክሩ ተለያዩ የአገራት ምሁራን ገለጹ፡፡ በጅማ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ሀገራት ምሁራን የተሳተፉበት በትምህርት ጥራት እና የእዉቀት ሽግግር ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ መድረክ እየተካሄደ ነዉ፡፡የእንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ኒዉዚላንድ፣ ህንድ እና የአፍሪካ አገራት ምሁራን በተሳተፉበት መድረክ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎች እና የምርምር ዉጤቶችን ምሁራኑ እያቀረቡ መሆናቸው ታውቋል፡፡በዚህ ፕሮግራም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ 300 የሚደርሱ የ2ኛ ዲግሪ እና ዶክትሬት ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በቢዝነስ፣ በህክምና ዘርፎችና በሌሎችም በተለይ የማስተማርና የዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑ ታውቋል፡፡የመድረኩ አስተባባሪ የአለም አቀፍ የእዉቀት ልዉዉጥ መረብ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር አማረ ደስታ እንዳሉት መድረኩ ለ10ኛ ጊዜ የተዘጋጀ በተለያዩ አለማት የሚገኙ ምሁራኖች በትምህርት ጥራትና እዉቀት ሽግግር ዙሪያ በጋራ የሚመክሩበት ነዉ፡፡ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ፕሮፌሰር አማረ ሌሎች የሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎችም ይህን መድረክ እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡የጅማ ዩኒቨርሲቲ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት አቶ ኮራ ጡስኔን በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲዉ ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ በዓለምአቀፉ የውይይት መድረክ ላይ እየተሳተፈ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ለሁለት ቀናት የሚቆየዉ ይህ ዓለምአቀፍ ኮንፍረንስ በቀረቡት የምርምርና የጥናታዊ ጽሑፎች ዙሪያ ዉይይት እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡ 
ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/32367/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e4bf577fbab5a0e3c48a48fc87942e1f
4e17b089c1cdb313bada8124eed14f18
ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ የኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ቦታን ጎበኙ
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 20 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ የፊታችን ቅዳሜ ለሚከበረው የኢሬቻ በዓል ያለውን ቅድመ ዝግጅት በዓሉ በሚከበርበት ቦታ ተገኝተው ተመልክተዋል።በጉብኝቱ ላይ የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ሃላፊ አቶ መለሰ አለሙም ተገኝተዋል።ምክትል ከንቲባ ዋ በዚሁ ወቅት በዓሉ የሚከበርበት ቦታ በሚገባ መዘጋጀቱን ተመልክተናል ብለዋል።የኢሬቻ በዓልን ስናከብር በዓለም ላይ ተከስቶ በርካታ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘውን የኮቪድ- 19 ጥንቃቄ መዘንጋት የለበትምም ነው ያሉት ።አያይዘውም በዓሉ ለኮቪድ 19 ጥንቃቄ ማድረግ በሚያስችል መልኩ እንዲከበር ከአባገዳዎች ጋር በመሆን ዝግጅቱ መጠናቀቁን ተናግረዋል።የመስቀል በዓልን ከህዝቡ ጋር በመሆን በጥንቃቄ ና በሰላም እንዲከበር መደረጉንም አስታውሰዋል።የኢሬቻ በዓል ሲከበርም እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ህዝቡ ከጸጥታ ሃይሉ ጋር በመሆን አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግም ምክትል ከንቲባዋ ጥሪ አቅርበዋል።የአዲስ አበባ ብልጽግና ፓርቲ ሃላፊ አቶ መለሰ አለሙ በበኩላቸው ÷ የኢሬቻ በዓል የሰላም፣ የአብሮነት፣ የፍቅርና የአንድነት በዓል እንደመሆኑ መልካም እሴቱን በጠበቀ መልኩ በሰላም እንዲከበር በየደረጃው የሚገኘው አመራር አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን ተናግረዋል።አያይዘውም ህዝቡም በዓሉ በሰላም እንዲከበር የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል የኮቪድ 19 በተከሰተበት ወቅት በመሆኑ ከሌላው ጊዜ በተለየ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም አንስተዋል።በሃይማኖት ኢያሱየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%88%9d%e1%8a%ad%e1%89%b5%e1%88%8d-%e1%8a%a8%e1%8a%95%e1%89%b2%e1%89%a3-%e1%8a%a0%e1%8b%b3%e1%8a%90%e1%89%bd-%e1%8a%a0%e1%89%a4%e1%89%a4-%e1%8b%a8%e1%8a%a2%e1%88%ac%e1%89%bb-%e1%89%a0%e1%8b%93/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b8e302db600c84ac4cdafe9858f52494
b73446e9ae6215c699925efd5ad248f7
አንዳንድ ሱዳናዊያን ሴቶች ሰርጋቸው አንድ ወር ገደማ ሲቀረው ይገረዛሉ። ከዛ ቀደም የተገረዙ ቢሆንም እንኳን በድጋሚ ይገረዛሉ። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ሴቶቹ ድንግል እንደሆኑ ማስመሰል ስላለባቸው ነው።
ለማግባት ሲሉ ለመገረዝ የተገደዱ ሱዳናውያን ሴቶች\nሱዳን ውስጥ ከአራት እስከ አስር ዓመት ባለው የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሴቶች ይገረዛሉ። በተለይም በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ዘንድ ሴቶች ሲገረዙ የብልታቸው ከንፈር ይቆረጣል፤ ብልታቸው እንዲጠብ ይሰፋል። ይህ ስፌት የሚለቀው የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሲፈጽሙ ነው። 87 በመቶ የሚደርሱ ከ14 እስከ 49 ዓመት የሚሆናቸው ሱዳናዊያን ሴቶች እንደተገረዙ የተባበሩት መንግሥታት ሰነድ ያሳያል። አንዲት ልታገባ ያለች ሴት ከሰርጓ በፊት ልትገረዝ ከሆነ ብልቷ በድጋሚ እንዲሰፋ ይደረጋል። የግርዛት አይነቶች "ለቀናት መራመድ አልቻልኩም ነበር" ማሀ (ለዚህ ታሪክ ሲባል ስሟ ተቀይሯል) የተገረዘችው ከሠርጓ ከሁለት ወር በፊት ነበር። ያገባችው ከእሷ በእድሜ በመጠኑ የሚበልጥ ሰው ነበር። "በጣም ያም ነበር። እናቴ መገረዜን እንድታውቅ ስላልፈለግኩ እስካገግም ድረስ ለቀናት ከጓደኛዬ ጋር መቆየት ነበረብኝ፤ በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ቀናት ለመራመድ ተቸግሬ ነበር፤ መሽናትም ከብዶኝ ነበር።" • ያለእድሜ ጋብቻን በእግር ኳስ የምትታገለው ታዳጊ ማሀ እንደምትለው፤ ባለቤቷ ከጋብቻ በፊት ወሲብ እንደፈጸመች ቢያውቅ በእሷ ላይ እምነት አይጥልም። "ከመጋባታችን በፊት ወሲብ እንደፈጸምኩ ካወቀ በእኔ ላይ እምነት ማሳደር ያቆማል፤ ከቤት እንዳልወጣ ሊያግደኝ፣ ስልኩን እንዳልጠቀም ሊከለክለኝም ይችላል።" የዩኒቨርስቲ ምሩቋና በ20ዎቹ እድሜ ክልል የምትገኘው ማሀ ያደገችው ግርዛት በተከለከለበት ሰሜናዊ ሱዳን ሲሆን፤ የምትሠራውም ግርዛት ሕጋዊ በሆነባት በመዲናዋ ካርቱም ነው። ማሀ ከሠርጓ በፊት በድብቅ በአዋላጅ ለመገረዝ ወደ ትውልድ ቀዬዋ ተመልሳ ነበር። ማሀና አዋላጇ ይተዋወቃሉ። አዋላጇ ማሀን በ5 ሺህ የሱዳን ፓውንድ (3,190 ብር ገደማ) ለመግረዝ ተስማሙ። "የምገርዘው ብር ለማግኘት ነው" በበርካታ ማኅበረሰቦች ባህል ሴቶች እስኪያገቡ ድንግል እንዲሆኑ ይጠበቃል። ሴቶች ሊያገቡ ሲሉ በቀዶ ህክምና ድንግል እንደሆኑ ለማስመሰል የሚገደዱትም ለዚሁ ነው። ሀይመኖፕላስቲ "hymenoplasty" በመባል የሚታወቀው ቀዶ ህክምና ሱዳን ውስጥ አይሰጥም። አንድ ክሊኒክ ደግሞ ለባለትዳር ሴቶች ብቻ ቀዶ ህክምናውን ይሰጣል። • የሴት ልጅ ግርዛት ምንድነው? የት እና ለምን ይፈጸማል? ሱዳናዊያን ሴቶች ብልታቸው ተሰፍቶ እንዲጠብ ከማድረግ ውጪ አማራጭ የላቸውም። አዋላጆቹ የሴቶችን የብልት ከንፈር ይቆርጣሉ፤ ሰፍተውም እንዲጠብ ያደርጋሉ። ግርዛትን ለማስቆም የሚንቀሳቀሱት የማህጸን ሀኪም ዶ/ር ሳዋን ሰኢድ፤ "የሴት ልጅን የመራቢያ አካል መስፋትም ሆነ መብሳት ግርዛት ነው" ይላሉ። የሱዳን የህክምና ባለሙያዎች ማኅበር ግርዛትን ስለከለከለ በካርቱም የሚገኙትን ጨምሮ በሌሎች ሆስፒታሎች ውስጥም ግርዛት አይካሄድም። ሲገርዙ የሚገኙ አዋላጆች ከሥራቸው ይባረራሉ፤ የህክምና መሣሪያቸውም ይወሰዳል። ይህንን ጽሑፍ ያጠናቀረችው ጋዜጠኛ በጎበኘቻቸው ሦስት ሆስፒታሎች ውስጥ ያገኘቻቸው አዋላጆች ግን ሴቶችን ለመግረዝ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸውላታል። ከአዋላጆቹ አንዷ ለጸሐፊዋ እንደነገረቻት፤ አንዳንዴ ሴቶችን የምትገርዘው ገንዘብ ለማግኘት ስትል ነው። "በቅርቡ የ18 ዓመት ልጅ ገርዣለሁ (የኢንፊቢዩሊሽን ግርዛት)፤ ታዳጊዋ በአጎቷ ልጅ ተደፍራ ነበር። እናቷ እያለቀሱ ስለነበር ልርዳቸው ብዬ ገረዝኳት። በ'ሳሊም ኢኒሺየቲቭ' ሴቶችን ላለመግረዝ ቃል ብገባም፤ የልጅ ልጆቼን ለማሳደግ፣ የትምህርት ቤት ወጪያቸውን ለመሸፈን ገንዘብ ስለምፈልግ ገርዣታለሁ።" 'ሳሊም ኢኒሺየቲቭ'፤ እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በ2008 ግርዛትን ለመግታት በተባበሩት መንግሥታት የተጀመረ ፕሮጀከት ነው። • የሴት ልጅ ግርዛት በከፍተኛ ደረጃ ቀነሰ ሱዳን...
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
a61564c35bc4e055c9b0271bdbd37a49
078bdb31b648fe51196e5fde179e52ed
ፕሬዚዳንት አልበሽር የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካን ጎበኙ
ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር የሙከራ ምርት የጀመረውን የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካ ጎበኙ።በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት ፕሬዚዳንት አልበሽር ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በመሆን ነው ፋብሪካውን ትናንት የጎበኙት።ግንባታው ሁለት ዓመት የፈጀው የኦሞ ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካ በቅርቡ በሙከራ ደረጃ ማምረት መጀመሩ ይታወቃል።ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል ስኳር 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል በዓመት ያመርታል ተብሎ ይጠበቃል።በቻይና ኩባንያ የተገነባው ፋብሪካው የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ስር እየተገነቡ ካሉት አራት ፋብሪካዎች ውስጥ ወደ ስራ በመግባት ቀዳሚ መሆኑን ኢቢሲ ዘግቧል።
ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/29007/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8201b81c7ba6950f04b1862be338aabe
266ec7d46d7fc002a81a13f469076906
ጫማ (የርዝመት አሀድ)
ጫማ አለም አቀፍ የርዝመት መለኪያ አሀድ ነው። በአለም ላይ ጫማ የተለያየ መጠን ያለው ቢሆንም በዋናነት የሚታወቀውን ከሌሎች የርዝመት መለኪያ አሀዶች ጋር ለማነጻጸር 1 ጫማ ከአንድ ሶስተኛ (0.3) ያርድ፣ 12 ኢንች፣ 0.3.480 ሜትር ጋር እኩል ነው። ሌላው የጫማ አይነት የሰርቬይ ጫማ የሚባለው ሲሆን 1 የሰርቬይ ጫማ ከ0.3048006 ሜትር ጋር እኩል ነው። የርቀት መለኪያ
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
b1de846c5af9aa90d996a5e52a1f7b72
a2d2f2b0cf3b155127ad335fac32e308
የኮሮና ወረርሽኝ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃንን ህልውና ስጋት ላይ ጥሏል
በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ማስታወቂያ የሚያስነግሩ ድርጅቶች በመቀነሳቸው፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉንና ተቇማቱ የስራ ማስኬጃ የገንዘብ እጥረት እየገጠማቸው በመሆኑ፣ ለሰራተኛ ደሞዝ ካለመክፈል አንስቶ ከገበያ እስከመውጣት የሚያደርስ ችግር ላይ መውደቃቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክርቤት የኢትዮጵያ ሲቪክ መረጃ ጥምረት ከተሰኘ የበጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች ስብስብ ጋር በመሆን ባጠናው ጥናት፣ በኮቪድ 19 ምክንያት የመገናኛ ብዙሃን ከማስታወቂያ ገቢ ያገኙ የነበረውን 60 በመቶ ገቢያቸውን ማጣታቸውን አሳይቷል። ጥናቱ፣ ባለፈው ሚያዝያ ወር ብቻ አንድ የህትመት መገናኛ ብዙሃን ስራውን ለማቆም መገደዱንና ሌላ የቴሌቪዥን ጣቢያ ደግሞ ከስርጭት ውጭ መሆኑንም ጥቁሟል። በዚህ ጉዳይ ያናገራቸው የመገናኛ ብዙሃን ምክር ቤቱ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና በየሳምንቱ የሚታተመው የቁምነገር መፅሄት ዋና አዘጋጅ አቶ ታምራት ሀይሉ፣ እርሳቸው የሚመሩት የቁምነገር መፅሄትን ጨምሮ፣ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ሚዲያዎች ላይ፣ ለጋዜጠኞች ወረርሽኙን መከላከያ ግብዓቶችን ለማቅረብ አቅም ከማጣት አንስቶ ህትመትና ስርጭትን እስከማስተጏጎል የሚደርሱ ጉልህ ጫናዎች እያሳደረ መሆኑን ያስረዳሉ። በስሩ 2300 ሰራተኞችን የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በኮቪድ 19 ምክንያት ገቢያቸው በከፍተኛ ሁኔታ ካሽቆለቆሉት የመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ተቇማት መሃል አንዱ ነው። የድርጅቱ ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስልጠናና ጥናት ዘርፍ ሀላፊ አቶ አቤል አዳሙ እንደገልፁልን፣ በ2006 ዓ.ም. ወደ ኮሮፖሬሽንነት ከተቀየረ በኃላ በአብዛኛው በማስታወቂያ ገቢ የሚተዳደረው ድርጅት የኮሮና ቫይረስ ኢትዮጵያ ውስጥ ከመግባቱ በፊት ያገኝ ከነበረው ጠቅላላ ገቢ 40 በመቶ የሚሆነውን በማጣቱ ትልቅ ጉዳት ደርሶበታል። ለወራት የአለም ስጋት ሆኖ በቀጠለው የኮሮና ቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በኢትዮጵያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን፣ ግለሰቦች ሊያደርጏቸው ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች ከማሳወቅ አንስቶ ኮቪድ-19ኝን የተመለከቱ ወቅታዊ ዘገባዎችን ለማህበረሰቡ የማድረስ ሀላፊነት ተጥሎባቸዋል። ኮቪድ-19 ባሳደረው ተፅእኖ ምክንያት ግን ሀላፊነት የተጣለበት ሚዲያ፣ ህልውናው አደጋ ላይ ወድቇል የሚሉት የዘርፉ ባለሙያዎች ከመንግስት ድጋፍ እንዲደረግላቸው የመፍትሄ ሀሳብ ያሉትን ጨምረው ለጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ጥያቄ ማቅረባቸውን አቶ ታምራት ያስረዳሉ። በመንግስት የሚነገሩ ማስታወቂያዎች ክፍያን፣ የመንግስትና የግል ሚዲያዎች እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከመጠየቅ በተጨማሪም የሚዲያ ተቇማቱ ዝቅተኛ ወለድ ያለው ብድር እንዲመቻችላቸው፣ ለመጪዎቹ አምስት ወራት ከሰራተኞች ደሞዝ ላይ የሚቆርጡትን የስራ ገቢ ግብርና የጡረታ መዋጮ መጠቀም እንዲችሉ፣ የአምስት ወር የግብር እፎይታ ግዜ እንዲሰጣቸውና፣ ዓመታዊ የአገልግሎት ክፍያና የህትመት ክፍያን ማዘግየት እንዲችሉም ጠይቀዋል። የድጋፍ ጥያቄውን ለጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮና ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ካስገቡ ሶስት ሳምንት እንደሆናቸው የሚናገሩት አቶ ታምራት እስካሁን ግን ምንም ምላሽ እንዳላገኙ ይገልፃሉ። ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ፓርላማ የሆነው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በኮቪድ 19 ምክንያት የደረሰበትን ጉዳት አሳውቆ ከመንግስት ድጋፍ ቢደረግለትም ድጋፉ ጊዜአዊ ነው የሚሉት አቶ አቤል፣ የግሉም ሆነ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በተለይ በዚህ ወረርሽኝ ወቅት ካላቸው ትልቅ ሚና አንፃር ማንኛውም ረጂ አካል ሊደግፋቸው ይገባል ይላሉ። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከመከሰቱ ቀደም ብሎ የቢራ ምርቶች ማስታወቂያ በብሮድካስት መገናኛ ብዙሃን ላይ እንዳይተላለፉ በመደረጉ ና፣ የመንግስት ወጪ ለመቀነስ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ማስታወቂያቸውን በመንግስት ሚዲያዎች ብቻ እንዲነገሩ በመደረጋቸው የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እስከ 40 ከመቶ የሚሆነውን ገቢያቸውን ማጣታቸውን የሚገልፁት የሚዲያ ባለሙያዎቹ ኮቪድ 19 ተጨማሪ ማነቆ ሆኖ ህልውናቸውን ሳያጠፋው አስቸኯይ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/5525225.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
dc8c906ff086c4950dc3b775ae999713
2678b16712c949d7f704d29172e26154
በመንግሥት ላይ ከ172 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ያደረሱ ተቋማት እየተመረመሩ ነው
የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በ2008 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት፣ በመንግሥት ላይ ከ172.6 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል ተብለው በተጠረጠሩ አካላት ላይ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ፡፡ምርመራው እየተካሄደ ካለባቸው አካላት መካከል ጥቂት ግለሰቦች ከክፍለ ከተማና ከሌሎች ሠራተኞች ጋር በመመሳጠር፣ ከመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በድርጅት ስም የተከራዩትን ቤት በሁከት ይወገድልኝ ጥያቄ ካርታ በማውጣት፣ 6,263 ካሬ ሜትር (ግምቱ ከ78.6 ሚሊዮን ብር በላይ) የሆነ ቦታን የግል በማድረግ ከተፈጸመ ወንጀል ጋር የተያያዘው ይገኝበታል፡፡በኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የሕንፃ ግንባታ ሥራዎች፣ የማሽነሪ ግዥና ተከላ ሥራ ከሕግና ከመመርያ ውጪ በመፈጸሙ፣ በመንግሥት ላይ ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት መድረሱ በተሰጠ ጥቆማ ኮሚሽኑ ምርመራ እያካሄደ እንደሆነ አስታውቋል፡፡በመድኃኒት ፈንድ ኤጀንሲም እንደዚሁ የኤችአይቪ መመርመሪያ መሣሪያ ግዥ ላይ ከሕግ ውጪ የተወሰኑ አቅራቢዎችን በማሳተፍና ግዥ እንዲፈጸም በማድረግ፣ በመንግሥት ላይ የ20 ሚሊዮን ብር ጉዳት አድርሰዋል በተባሉ አምስት የመሥሪያ ቤቱ ሠራተኞች ላይ ኮሚሽኑ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ገልጿል፡፡እንዲሁም በኮንስትራክሽን ዘርፍ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 እየተሠራ ላለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለ 11 ፎቅ ሕንፃ ግንባታ የማሽነሪና የግንባታ ዕቃ ማስቀመጫ ቦታ ለኮንስትራክሽን ድርጅቱ በሊዝ መሰጠት ሲገባው በነፃ በመፈቀዱ፣ መንግሥት ከሊዝ ማግኘት የሚገባውን 22 ሚሊዮን ብር በማጣቱ ጉዳዩ በኮሚሽኑ እየተመረመረ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡በተመሳሳይ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከመካነ ሰላም - ግንደ ወይን በሚገነባ መንገድ ሥራ ላይ ሲጂጂሲ ከተባለ የቻይና ድርጅት ጋር ከተደረገው የኮንትራት ስምምነት ውጪ፣ ያላግባብ 12 ሚሊዮን ብር ተከፍሏል በሚል በቀረበ ጥቆማ ላይ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምርመራ እያካሄደ ከሚገኝባቸው ተጠቃሾቹ ናቸው፡፡የምርመራውና የማስረጃ ማሰባሰቡ ሥራ እንደተጠናቀቀ ክስ እንደሚመሠረትና ጥፋተኛ መሆናቸው በፍርድ ቤት ሲረጋገጥ፣ ኮሚሽኑ ንብረት የማስመለሱን ተግባር እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡   
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/article/9562
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8a8b5b4dad136aba5c4d6cb2eb4be72b
1029f3fda78ec847464481e57bb06a2e
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በስልክ ተወያዩ
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በስልክ ተወያዩ።ሁለቱ መሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር 302 ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች ቤተሰቦች የኀዘን መግለጫ ተለዋውጠዋል።ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጠንካራ ተቋም መሆኑን አድንቀው በተፈለገበት ቦታ ሁሉ የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ፈቃደኝነታቸውን አስታውቀዋል።ፕሬዝዳንቱ በማስከተልም በኢትዮጵያ ባለፉት ወራት ለተካሄዱ ሁሉን አቀፍ ለውጦች ያላቸውን ድጋፍ ገልፀዋል።ሁለቱ መሪዎች በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ረጅም ጊዜ የዘለቀ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል፡፡ (ምንጭ፡-የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት)
ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/32313/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
0069e462e0d726e6b4a0e25246ea3ce1
70654306e945e48b44be2d6a463a04c7
ቀን አሥራ ስምንት
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር ሃገሪቱ ከሜክሲኮ ጋር የምትዋሰንበት የደቡብ ድንበር አካባቢ ያለው ሁኔታ የማይቀር “የሰብዓዊና የብሄራዊ ፀጥታ ቀውስ” ነው የሚል ዕምነት ለማሥረፅ በብርቱ እየገፋ መሆኑ ተገልጿል።የፕሬዚዳንቱ አቋም ከሕዝብ እንደራሴዎቹ ጋር ለገቡበት የወሰን አጥር ግንባታ ሃሣባቸው ድጋፍ ለማግኘት እንደሆነ ነው የሚሰማው።በዚሁ በፕሬዚዳንቱና በእንደራሴዎቹ መካከል በተፈጠረው ፍጥጫ ምክንያት የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት በከፊል ከተዘጋ ዛሬ አሥራ ስምንተኛ ቀኑን ደፍኗል።ፕሬዚዳንት ትረምፕ ይህንኑ የደቡብ ድንበር ግንብ ሃሣባቸውን ለማስረገጥ አስበውበታል የተባለ ንግግር ዛሬ ምሽት ላይ በቴሌቪዥን ያደርጋሉ ተብሏል። ከነገ በስተያ ሐሙስ ደግሞ ወደ ወሰኑ አካባቢ እንደሚሄዱ ተነግሯል።በሌላ በኩል ግን የተወካዮች ምክር ቤቱ “ለፕሬዚዳንት ትረምፕ የጠየቁትን የግንብ ማሠሪያ ወጭ ቢፈቅድላቸው የተሣሣተ እርምጃ ይሆናል” ሲሉ ዛሬ ኒው ዮርክ ላይ ለተሰበሰቡ ታዳሚዎች ንግግር ያደረጉት የሕግ ወመሰኛ ምክር ቤቱ ዴሞክራቲክ መሪ ቸክ ሹመር አመልክተዋል።“ሃገር ማስተዳደር እንዲህ አይደለም። ቡጢ ጨብጠህ ጠረጴዛ እየደበደብክ እኔ ያልኩት ካልሆነ እያልክ ለሚሊዮኖች መጎዳት ምክንያት በመሆን አይደለም። ሕገመንግሥቱ እንዲያ አይልም። ምርጫዎች መዘዝ እንደላቸው ይታወቃል። ሪፐብሊካኑ የሕግ መምሪያውንም የሕግ መወሰኛውንም ተቆጣጥረው በነበሩበት ጊዜ እንኳ ፕሬዚዳንቱ ይህንን ግንብ የማቆም ሃሣባቸውን ማስፀደቅ አልቻሉም። ምክንያቱም መጥፎ ሃሣብ መሆኑን እንደራሴዎቹ ያውቁ ስለነበረ ነው። አሁን ታዲያ ምንም እንኳ ፕሬዚዳንቱ ባለፈው ምርጫ የሕዝብ ይሁንታ ተነፍገው የተወካዮች ምክር ቤቱን ከእንግዲህ ባይቆጣጠሩትም መንግሥቱን ዘግተውታል” ብለዋል ሴናተር ሹመር።በፕሬዚዳንቱና በዴሞክራቲክ እንደራሴዎቹ መካከል በተፈጠረው መፋጠጥ መንግሥቱ ከተዘጋ ወደ ሦስተኛ ሣምንቱ ቢገባም እስከአሁን ከተካሄዱ ድርድሮች የተጨበጠ ተስፋ ሰጭ ውጤት የለም።የዩናይትድ ስቴትስን ሩብ መንግሥት የዘጋው የአሁኑ ሁኔታ ወደ ፍፃሜው የመጠጋት አዝማሚያም እየታየ አይደለም።ስምንት መቶ ሺህ የሚሆኑ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ሠራተኞች አንድም ከሥራቸውና ከክፍያ ውጭ ሆነዋል፤ አልያም ያለክፍያ እየሠሩ ናቸው።
ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/us-shutdown-border-1-8-2019/4734085.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
ba89894053fb4c407b57be06e93ab0a4
9cdb90956f388f1367e4ff8f0a428b05
ከ32 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጤና መድህን ሽፋን ተጠቃሚ መሆናቸው ተነገረ
ከ32 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጤና መድህን ሽፋን ተጠቃሚ መሆናቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደስ ገለጹ። በአማራ ክልል የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከልና የጤና መድህን ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የንቅናቄ ዘመቻ ውይይት እየተካሄደ ሲሆን፤ በውይይቱ የክልሉ ርዕሸ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር፣የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ ሃላፊዎች እንዲሁም የዞንና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።በዚህ ወቅት ዶክተር ሊያ ባደረጉት ንግግር፤ የጤና መድህን ሥርዓት በገጠርና በከተሞች መደበኛ ባልሆነው የኢኮኖሚ ዘርፍ ተሠማርተው ለሚገኙ ዜጎች ተጠቃሚነትን የሚረጋግጥ ሥርዓት መሆኑን ገልጸዋል። የሁሉን አቀፍ የጤና መድህን ሁለት ዋና ዋና ዓላማዎች እንዳለው የገለጹት ዶክተር ሊያ አንደኛው ከኪስ በሚወጣ ወጪ ለሚታከሙ ዜጎች ለድህነት እንዳይጋለጡና አስፈላጊውን የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ተናግረዋል።ሁለተኛው የጤና ስርዓት ዘላቂ የሆነ የገቢ ምንጭ እንዲኖረው በማድረግ ትልቅ ሚና የሚጫወት ፕሮግራም ለማድረግ ያለመ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ በሀገር ደረጃ በ2003 ዓ.ም በ13 ወረዳዎች ተጀመረው የጤና መድህን ሥርዓት በ2012 ዓ.ም በ770 ወረዳዎች ተተግብሮ 32 ሚሊዮን ዜጎች የጤና መድህን ሽፋን ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ብለዋል። ከአባላቱም 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን በመግለጽ፤ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች በጤና መድህኑ ወጪ ተሸፍኖላቸው የህክምና ጤና አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል። የጤና መድህኑ በሀገር አቀፍ ደረጃ አባላት በማፍራት ያለው አፈፃፀም 82 በመቶ ሲሆን በአማራ ክልል ያለው አፈፃፀም ደግሞ 92 መሆኑን ገልጸዋል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እንደ ሀገርና ክልል ስርጭቱ እና ወደ ፅኑ ህሙማን የሚገቡ የኮሮና ቫይረስ ህሙማን ቁጥር እየጨመረ የመጣ በመሆኑ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም ሚኒስትሯ አሳስበዋል:: የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መልካሙ አብቴ በበኩላቸው፤ የተቀዛቀዘውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የመከላከል ስራና የጤና መድህን ተደራሽነት ለማረጋገጥ ከጥር 1 እስከ 30 ቀን 2013 ዓ.ም የአንድ ወር የንቅናቄ ዘመቻ በአማራ ክልል እንደሚካሄድ ተናግረዋል:: የክልሉ ርዕስ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር በኩላቸው፤ ህብረተሰቡ በሠላም ማስከበር ያደረገውን የተቀናጀ ስራ የኮሮና ቫይረስን በመከላከልና የጤና መድህን ተደራሽነትን በማረጋገጥ ሊደግመው እንደሚገባ ገልጸዋል::የክልሉ መንግስት ከዚህ በፊት ሲያደርገው እንደነበረው ሁሉ አሁንም የኮሮና ቫይረስን የመከላከል እና የጤና መድህን ተደራሽነትን የማረጋገጥ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን የዘገበው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ነው::አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20 /2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=38384
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c6d9998bff1ba7732515b6b5ff8877a8
f026dfd84bc7fdbfce6634abd1bc8ebc
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና ፋሲል በይፋ የቅጥር ውል ተፈራርመዋል
ፋሲል ከተማ የአዲሱ አሰልጣኙን ቅጥር እና ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ ዛሬ ረፋድ ላይ በኢትዮጵያ ሆቴል መግለጫ ሰጥቷል።ከተጠራበት ሰዓት ዘግየት ብሎ በጀመረው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የክለቡ ሶስት የቦርድ አባላት እና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በአንድነት በመሆን ለአንድ ሰዐት ያህል በስፍራው ከተገኙ ጋዜጠኞች ጋር ቆይታ አድርገዋል። በመርሀ ግብሩ መጀመሪያ ስለክለቡ ወቅታዊ ሁኔታ ገለፃ ያደረጉት የክለቡ ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አስቻለው ወርቁ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በገለፃቸውም የክለቡን ደረጃ ለማሳደግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አስረድተው ከስያሜው በመጀመርም የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ በሚል መጠሪያ እንዲጠቀም ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልፀዋል። ከዚህ በተጨማሪ በሀገር ውስጥ እና በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በተወሰደ ተሞክሮ የክለቡን መዋቅራዊ አደረጃጀት በመቀየር ለስራ አኪያጅ እንዲሁም ለቴክኒክ እና አስተዳደር ክፍሎች የሚሆኑ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች በቅጥር የሚገቡበት መስፈርት እንደተዘጋጀ አስረድተዋል።በቀጠል አቶ አስቻለው የዚሁ ለውጥ የመጀመሪያ እርምጃ ለሆነው የአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ቅጥር ምክንያት የሆኑ ነገሮችን አስረድተዋል። እንደሳቸው አገላለፅ አሰልጣኙ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቷ ካሉ ስመጥር እና ብቃት ያላቸው አሰልጣኞች አንዱ በመሆናቸው ክለቡን ካለበት ደረጃ ከፍ ያደርጋሉ ብለው እንዳመኑ እና በጎንደር እና በአካባቢው ያሉ ወጣቶችን በማብቃት ወደ ትልቅ ተጨዋችነት ማሳደግ ላይም የራሳቸው አስተዋፅኦ እንደሚያደርጉ በማሰብ እንዲሁም የደጋፊውን ጥሩ እግር ኳስ የሚጫወት ውጤታማ ቡድን የማየት ህልም እንደሚያሳኩ በማመን ቅጥሩን መፈፀማቸውን አስረድተዋል። ” ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ በሰበሰብነው መረጃ አሰልጣኝ ውበቱ በደጋፊዎቻችን ተቀባይነት አላቸው። እንደ ዕድል ሆኖ የቀደሙት አሰልጣኛችን አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪም በሙያው ስነምግባር የታነፁ እና ተግባብተው መስራት የሚችሉ ነበሩ። አሁን ደግሞ ቡድኑ ከሚፈልገው ውጤት አንፃር አቶ ውበቱን ለአሰልጣኝነት መርጠናል።” ያሉት ምክትል ሰብሳቢው ስለቀጣይ ዕቅዶች ሲናገሩም ” በቀጣይነት አሰልጣኝ ውበቱ ስራቸውን ከጀመሩ በኋላ ክለቡን ማጠናከር ቀዳሚ ስራችን ይሆናል። የፋይናንስ አቅማችንን ለማጎልበት የገቢ ማሰባሰቢያ እና ሌሎች አማራጮችንም እንተገብራለን። ከዚህ በተጨማሪ ቡድኑ ያለንበትን ክፍተቶች ባማከለ ሁኔታም ተጨዋቾችን እናስፈርማለን። በቀጣይም እስከ መስከረም ባለው ጊዜ ወደ ኤርትራ ተጉዘን ለምናደርገው የወዳጅነት ጨዋታም እንዘጋጃለን።” ብለዋል።ቀጥሎ ንግግር የማድረግ ዕድል ያገኘው ዋንጫ የማንሳት እና መገለጫ ያለው አጨዋወትን የሚከተል ቡድን የመገንባት ሀላፊነት የተጣለበት አሰልጣኝ ውበቱም ” ከሐምሌ 1 ጀምሮ ወደ ፋሲል ለመምጣት ተስማምቻለው። የተለያዩ ጥያቄዎች ቢደርሱኝም ቀጣይ ማረፊያዬን ረጋ ብዬ በማሰብ ጠንካራ ደጋፊ ያለው እና እኔ ለምመርጠው አጨዋወት የሚመቹ ነገሮችን ያሟላ ክለብ መሆኑን ተገንዝቤ ቀጣዮቹን ሁለት አመታት አብሪያቸው ለመቆየት ወስኛለው። በዚህም ደስታ ይሰማኛል። በቆይታዬም ከአመራሩ ጋር በመተባበር የሚጠበቅብኝን ለማድረግ ጥረት አደርጋለው። ለኔም ለክለቡም መልካም የስራ ጊዜን እመኛለሁ። ” በማለት በወር የተጣራ ስልሳ ሽህ ብር እና በድርድር ላይ ያሉ ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን ስለሚያስገኝለት አዲሱ ስራው ተናግሯል።ከዚህ በኋላ ከጋዜጠኞች በርካታ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን የቦርድ አመራሮቹ ምላሾችን ሰጥተዋል። ወጣቶችን የማሳደግ ስራ ከአሰልጣኙ የስራ ጊዜ ማጠር ጋር ሊተገበር የሚችልበት መንገድ ላይ ለተነሳው ጥያቄ በስፍራው ካሉ ፕሮጀግቶች ጋር ቀርቦ የሚሰራ እና ለታዳጊዎች የእድገት መንገዱን የሚያመቻች የቴክኒክ ዳይሪክተር ቅጥር እንደሚፈፀም የተነገረ ሲሆን ሌላኛው የቦርድ አባል አቶ እሸቱ ያድጎ ባነሱት ሀሳብም ” ከአሰልጣኙ ጋር የሚኖረን ቆይታ በሁለት አመት የሚቋጭ አይሆንም። በቀጣይ ጊዜያትም ውል የማራዘም አማራጭ አለን። አሁን ባለው ሁኔታ ከታች በሚመጡ ተጨዋቾች ብቻ ውጤት ማምጣት ከባድ ነው። ስለዚህም ባሉን ተጨዋቾች በይሸፈኑ ቦታዎች ላይ ግዢዎችን እንፈፅማለን። በሂደት ግን ወጣቶችን በማሳደጉ ላይ እናተኩራለን። ምንም አይነት አማራጭ ካላገኘን በቀር ግን ተጨዋቾችን ከውጪ የማምጣት ሀሳብ የለንም። ይሉትም ከጥቂቶቹ በቀር ከክለቡ ጋር አይቀጥሉም። ” ሲሉ ተደምጠዋል።ለተጨዋቾች በሚያወጡት የተጋነነ ክፍያ ምክንያት ክለቦች ላይ እየተፈጠረ ካለው ጫና አንፃር የፋሲልን ዝግጅት ምን እንደሚመስል ተጠይቀው የመለሱት አቶ አስቻለው ደግሞ ” የክለባችን የፋይናንስ ምንጮች ከተማ አስተዳደሩ እና ወረዳዎች ፣ ስፖንሰሮቻችን እንዲሁም የደጋፊ ማህበሩ መዋጮ ናቸው። ከነዚህ ውጪም በሌሎች ገቢ የማሰባሰቢያ ሂደቶች ራሳችንን እናጠናክራለን። አሁንም ባለን አቅም ልክ ነው ውሎችን የምንፈፅመው በመሆኑም ጫና አይኖረውም። በተጨዋቾች ዝውውር ጉዳይ ላይ ለመወሰን ደግሞ የክለቦችን እና የገበያውን አካሄድ በማየት ላይ እንገኛለን። ” ብለዋል።አሰልጣኝ ውበቱም ለሱ በተነሱት ጥያቄዎች ዙሪያ እንዲህ ሲል ጠቅለል ባለ መልኩ ምላሽ ሰጥቷል። ” ለአራት አመት ኮንትራት ነበር ያናገሩኝ። ሆኖም እኔ አልተቀበልኩትም። በርግጥ አንድ ቦታ ላይ መቆየት የተሻለ ስራ ለመስራት ይረዳል። ነገር ግን የፌዴሬሽኑ የአሰልጣኞች ውል ብዙ ነፃነት አይሰጥም። የስራ ዋስትናንም የሚፈታተን ስለሆነ በረጅም ጊዜ ውል መታሰርን ከባድ ያደርገዋል። ሆኖም በየትኛውም ጊዜ ለማራዘም ውሉ የሚሰጠን ክፍተት አለ። ታዳጊዎችን በተመለከተ እኔ መሰረቱን የመጣል ድርሻ ነው ያለኝ ከዛ ግን እኔ ብቆይም ባልቆይም ክለቡ ሊያስቀጥለው ይችላል። በተረፈ ምክትል አሰልጣኞቼን በራሴ የመምረጥ ነፃነት ተሰጥቶኛል። በሀገራችን ባለው ሁኔታ ምክትል አሰልጣኞች ለዋና አሰልጣኞች አለመረጋጋት ምክንያቶች ናቸው። እንደሌላው አለም አሰልጣኝ ሲወጣ አብረው ስለማይወጡ ለነሱ የስራ ዕድል እንደመክፈት የሚታይ ነው። ስለዚህ ይህ ነፃነት ሲሰጠኝ አብረውኝ በሙሉ ሀላፊነት ከሚሰሩ ችግር ሲኖር ደግሞ አብረውኝ ከሚሰናበቱ ሰዎች ጋር ነው የምሰራው። በስራ ህይወቴ በርካታ ደጋፊዎች ካላቸው ክለቦች ጋር ስለሰራው ጫና ውስጥ አልገባም። ”የዕለቱ መርሀ ግብር ከመጠናቀቁ በፊትም ሁለቱ አካሎች ውሉን የተፈራረሙ ሲሆን አሰልጣኙም የክለቡን አርማ ይዘው ፎቶ ተነስተዋል።
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/38572
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
1646a9fa0ad8fae7cc49e6edbd9c3881
f7d94cd150fa33760b2e090502c15d65
የዊል ስሚዝ ባለቤት ስለነበራት የፍቅር ግንኙነት በቀጥታ ስርጭት ላይ ተናገረች
ሬድ ቴብል ቶል በተሰኘው የፌስቡክ ቀጥታ ስርጭቷ ላይ ነው ወ/ሮ ፒንኬት ለባለቤቷ ምስጢሩን የዘረገፈችው። ነገር ግን፤ ጃዳ ፒንኬት ከአልሲና ጋር ግንኙነት የነበራት ከዊል ስሚዝ ጋር ተቆራርጠው ሳለ እንደነበር ይፋ አድርጋለች። "ከዚያ በኋላ ተለያይተናል" ስትል ነገሩ በጊዜው እንደተቋጨ አሳውቃለች። "ከዚያ በኋላ ባለው ጊዜ ከኦውገስት ጋር የተለየ ግንኙነት ነው ያለን" ብላለች። "በወቅቱ ጥሩ ሁኔታ ላይ አልነበርኩም። ልቤ ተሰብሮ ነበር" ስትል የነበረችበትን ሁኔታ ገልፃለች። ዊል እና ጃዳ ፒንኬት ስሚዝ ከአውሮፓውያኑ 1997 ጀምሮ በትዳር ኖረዋል። ሁለት ልጆችም አፍርተዋል። ጥንዶቹ በቅርቡ ተለያይተው እንደገና እንደተጣመሩ ይፋ አድርገው ነበር። ጥንዶቹ፤ ማኅበራዊ ድር-አምባዎች ላይ እየተነዙ የተለያዩ አወዛጋቢ ወሬዎችን ለማጥራት ነው ሐቁን ለመናገር የወሰንነው ብለዋል። የማኅበራዊ ድር-አምባ ተጠቃሚዎች ስለ ጥንዶቹ ትዳር ማውራት የጀመሩት ኦውገስት የተሰኘው 'ራፐር' አንድ የራድዮ ዝግጅት ላይ ቀርቦ ፍንጭ የሚሰጥ ነገር ከተናገረ ወዲህ ነው። ኦውገስት አልሲና ከጃዳ ፒንኬት ጋር የነበረውረውን ግንኙነት ዊል ስሚዝ እንደሚያውቅና ይህ ደግሞ ጥንዶቹ በይፋ ከሌሎች ሰዎች ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል የተዛባ ነገር ፈጥሮ እንደነበር ተናግሯል። ጃዳ ፒንኬት ስሚዝ የአጭር ጊዜ የፍቅር ጓደኛዋ ኦውገስት ትዳሯ ላይ ችግር እፈጥራለሁ የሚል ስጋት እንነበረው ትናገራለች። ነገር ግን "እኔና አንተ በፈቃደኝነት ስለሆነ የተለያየነው እሱ ምንም አላጠፋም" ስትል ለባለቤቷ ተናግራለች። ዊል ስሚዝ፤ ምንም እንኳ ተለያይተው የነበረ ቢሆንም በወቅቱ ባለቤቷ ለምን ወደ ሌላ ወንደ እንደሄደች ጠይቋታል። "በቃ ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ እፈልግ ነበር" ብላ ስትመለስ ዊል ስሚዝ በመስማማት ፊቱን ሲነቀነቅ በምስሉ ላይ ይታያል። ጥንዶቹ ወደ ትዳራቸው ከተመለሱ በኋላ ፍቅራቸው "ገደብ የለሽ" መሆኑን ወ/ሮ ስሚዝ በቀጥታ ስርጭቱ ላይ አስታውቃለች። በስርጭቱ መጨረሻ ላይ ጥንዶቹ አይበሉባቸው ካገጫጩ በኋላ "አብረን እንጓዛለን፤ አብረን እንሞታለን። ትዳር እስከ መቃብር" ሲሉ ተደምጠዋል።
UNK
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
f9879004504506886ce03fc013651854
1f7cc3015ece28380d8786bf0c168a9a
ከፍተኛ ሊግ | ገላን ከተማ አዲስ አሰልጣኝ ቀጠረ
በፀሎት ልዑልሰገድ የከፍተኛ ሊጉ ተወዳዳሪ ገላን ከተማ አዲስ አሰልጣኝ በመሆን ተሹመዋል፡፡የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ረዳት አሰልጣኝ እንዲሁም በ2011 ኢትዮጵያ መድንን በመያዝ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ለማሳደግ ከጫፍ ደርሶ ሳይሳካላት የቀረ ሲሆን የተሰረዘውን የ2012 የውድድር ዓመት ደግሞ ኢኮሥኮን እያሰለጠነ ከቆየ በኃላ ዛሬ ረፋድ የገላን ከተማ ዋና አሰልጣኝ ሆኗል፡፡አሰልጣኙ ከሰሞኑ በክለቡ ውላቸው የተጠናቀቀ እንዲሁም አዳዲስ ተጫዋቾችን እንደሚያስፈርሙ ይጠበቃል፡፡
ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/61497
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
608eb12f4bd89dfe4594bc8b600fd784
5ad8997756ceb1d122b57e770f0c0754
በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች ወደ ሱዳን መሰደዳቸውን ቀጥለዋል ተባለ
ሱዳን ላልታጠቁ ስደተኞች በሯን ከፍታለችበትግራይ ክልል ያለውን ወታደራዊ ግጭት በመሸሽ በሺዎች የሚቆጠሩ የክልሉ ነዋሪዎች ወደ ጎረቤት አገር ሱዳን መሰደድ መቀጠላቸው ተገለጸ፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የስደተኞችና የሰብዓዊ ዕርዳታ አስተባባሪ ተቋም ሰሞኑን እንዳስታወቀው፣ በርካታ ኢትዮጵያውያን በትግራይ ካለው ወታደራዊ ግጭት ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ለማዳን፣ መኖሪያ ቀዬአቸውን ለቀው ወደ ሱዳን በመሰደድ ላይ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡በሱዳን የሚገኘው የዚህ ተቋም አስተባባሪዎች ከሱዳን መንግሥትና ሌሎች አጋር ሰብዓዊ ተቋማት ጋር በመሆን ስደተኞቹ በሱዳን መጠለያ እንዲያገኙ፣ ዕለታዊ ምግብና ውኃ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም አስታውቋል፡፡ እስከ ሐሙስ ኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ጥቂት ቀናት ብቻ ከሰባት ሺሕ በላይ ነዋሪዎች ከትግራይ ክልል ወደ ሱዳን መግባታቸውን ያስታወቀ ሲሆን፣ አብዛኞቹም ሴቶችና ሕፃናት እንደሆኑ ጠቁሟል፡፡ ስደተኞቹ ሱዳንና ኢትዮጵያን በሚያዋስኑት ከሰላና ገደሪፍ አካባቢዎች በሚገኙ የስደተኛ ካምፖች ጊዜያዊ መጠለያ እንዲያገኙ መደረጉንም ገልጿል፡፡ በ24 ሰዓት ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ከትግራይ ክልል ወደ ሱዳን መግባታቸውን ያመለከተው ተቋሙ፣ በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ግጭት እየተባባሰ በመሆኑ የስደተኞች ቁጥር በእጅጉ ሊያሻቅብ እንደሚችልም አስታውቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት የስደተኞች መጠለያ ካምፖች 96 ሺሕ ኤርትራዊያን ተጠልለው የሚገኙ መሆኑን ገልጾ፣ በክልሉ ከአንድ መቶ ሺሕ በላይ የሆኑ ነዋሪዎች ጦርነቱ ከሚካሄድባቸው አካባቢዎች ተፈናቅለው መሸሻቸውን አስታውቋል፡፡ በትግራይ ክልል የተጠለሉ ኤርትራዊያን ስደተኞች ሁኔታና በዚያው ክልል ከቀዬአቸው የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ እንዳሳሰበው በመግለጽ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ሰብዓዊ ዕርዳታ የሚሰጡ ተቋማት በትግራይ ክልል መንቀሳቀስ የሚችሉበትን ሁኔታ እንዲያመቻችም ጠይቋል፡፡ የሱዳን መንግሥት ቀደም ብሎ ከኢትዮጵያ በሚያዋስነው ድንበር ላይ ስድስት ሺሕ ተጨማሪ ጦር በማሥፈር ድንበሩን ዘግቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ የብሔራዊ ደኅነነት አማካሪ አድርገው በቅርቡ የሾሟቸውን አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ወደ ሱዳን መላካቸው ይታወሳል፡፡አቶ ገዱ የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይን መልዕክት ለሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ካደረሱ በኋላ፣ የኢትዮጵያ አዋሳኝ የሆኑ የሱዳን ድንበሮች ክፍት እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ የሱዳን መንግሥት ባወጣው መግለጫ በትግራይ ያለውን ሁኔታ ሸሽተው የሚመጡ ኢትዮጵያውያንን ሱዳን እንደምትቀበል፣ ነገር ግን የጦር መሣሪያ የታጠቁ ስደተኞችን ወደ ድንበሯ እንደማታስገባ አስታውቋል፡፡   
ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/20454
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification