input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
በኤኮኖሚው ረገድ በፋርስ ባህረ ሰላጤ በጋራ የሚያካሂዷቸው የነዳጅ ዘይት ሥራዎች እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን አይወዱትም።
|
ቀጠር ከሙስሊም ወንድማማቾች ማህበር ጋር ረዥም ጊዜ የዘለቀ ቅርብ ግንኙነት አላት።
|
ቡድኑ በጎርጎሮሳዊው ቱ የግብጽ ምርጫ ብዙ ድምጽ ሲያገኝ ቀጠር ከካይሮ ጋር ፖለቲካዊ ግንኙነትዋን ለማጠናከር ሞክራ ነበር።
|
የሳውዲ መንግሥት የሙስሊም ወንድማማቾች ማህበር ለአረብ ባህረ ሰላጤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ስርዓት አደጋ አድርጎ ነው የሚያየው።
|
በዚህ የተነሳም ቀጠር አሁን የተጠየቀችውን ሁሉ ማሟላት አስቸጋሪ ነው የሚሆንባት ይላሉ ዞንስ።
|
ወይም ደግሞ ከአረብ ወንድሞቿ ጋር ጋር እንደ እስካሁኑ ጥሩውን ግንኙነት አጠናክራ ልትቀጥልም ትፈልግ ይሆናል።
|
ከጥቂት ቀናት በፊት የቀጠር አምባሳደር በርሊን ውስጥ ቀጠሮች እና ሳውዲዎች በመሠረቱ አንድ ቤተሰብ ናቸው ብለው ነበር።
|
በዚህ ውዝግብ ውስጥ የሚካፈሉት ወገኖች ገጽታቸውን ሳያበላሹ ከዚህ ውዝግብ የሚላቀቁበትን መንገድ ነው የሚፈልጉት።
|
በዛም ሆነ በዚህ ግን ቀጠር የተጠየቀችውን ታሟላላቸው ብዮ አላስብም።
|
ውይይቱ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ሄደው ለመግባት የጠየቁ ወጣቶችም እርሱ እንደሚለ በልዩ ፖሊስ ተደብድበው ጉዳት ደርሶባቸዋል የታሰሩም አሉ ።
|
በውይይቱ ላይ ከህብረተሰቡ ለተነሱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልስ ሰጥተዋል።
|
የትኛውንም ወረዳ እንደማይወክሉ የተናገሩት እኚሁ ነዋሪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህብረተሰቡ ጥያቄዎች የሰጡት መልስ ከሞላ ጎደል ጥሩ ነው ብለዋል።
|
ሆኖም ጥያቄ የማቅረብ እድል አለማግኘታቸውን ተናግረው በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ አጥጋቢ መልሶች እንዳላገኙ መነሳት ነበረባቸው ያሏቸው ጥያቄዎችም እንዳልተነሱ ተናግረዋል።
|
ወደ ውይይቱ አዳራሽ መግባት ተከለከልኩ የሚል ሌላው ወጣት ደግሞ የአፋር ወጣቶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት ውይይት ላይ ለመካፈል ቢፈልጉም አለመጋበዛቸውን ይገልጻል።
|
ውይይቱ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ሄደው ለመግባት የጠየቁ ወጣቶችም እርሱ እንደሚለው በልዩ ፖሊስ ተደብድበው ጉዳት ደርሶባቸዋል የታሰሩም አሉ።
|
ከተጎዱት መካከል ሴቶች እና በእድሜ የገፉም እንደሚገኙበት ወጣቱ ተናግሯል።
|
በርሱ አባባል ወጣቶቹ ስብሰባው እንዳይገቡ የተከለከሉት በክልሉ ያለውን ችግር ያጋልጣሉ በሚል ስጋት ሳይሆን አይቀርም።
|
ዶቼቬለ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን የክልሉን ባለሥልጣናት ለማነጋገር ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።
|
አቶ ብሩክ መኮንን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ልዑክ ቃል አቀባይ ናቸው።
|
ባለፉት ሁለት አመታት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኩል የተጠኑ ጥናቶች አሉ።
|
የእነዚህ ጥናቶች አፈጻጸምን በሚመለከት ነው የዚህ ስብሰባ ዋና ትኩረት።
|
በአፈጻጸም ሒደቱስ መታየት ያለባቸው ጉዳዮች ምንድናቸው የሚለው ላይ ነው ይኸ ስብሰባ በዋናነት የሚያጠነጥነው።
|
ከትልልቆቹ ጥቆማዎች አንዱ ትኩረቱ ከሰላም ማስከበር ወደ ሰላም የማስፈን ተልዕኮ መሻገር አለበት የሚለው ነው።
|
የሰላም ማስፈን ተልዕኮ ስራ ግጭት የመከላከል እንቅስቃሴዎች የሰላም ግንባታ የድኅረ ግጭት መልሶ ማቋቋም እና የልማት ሥራን ያካትታል።
|
አንዱ ፈታኝ ነገር ሰላሙን ዘላቂ ለማድረግ ምንም ሥራ ሳይሰራ ወታደሮቹ እንዲወጡ መደረጉ ነው።
|
በቀውስ በተመቱ አገሮች በመንግሥታዊ አስተዳደር ውስጥ የሕግ የበላይነትን እና ሌሎች አገልግሎቶችን መልሶ ማስፈን ሌላው ችላ የተባለ ነገር ነው።
|
ግጭት የነበረባቸውን አካባቢዎች ስንመለከት መላ የጸጥታ ጥበቃ እና የፍትኅ ሥርዓቶቹ ፈርሰዋል።
|
ሪያና ፓኔራስ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ግጭት ባቀወሳቸው አካባቢዎች በወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ብቻ ተወስኖ ቆይቷል ሲሉ ይተቻሉ።
|
በ ገፆች የተቀነበበው ግምገማ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ የፖለቲካ ሒደትን የመደገፍ ሰፊ ሚና አንድ አካል ሊሆን ይገባል የሚል ጥቆማ ሰጥቷል።
|
የተባበሩት መንግሥታት በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎቹ መስክ ተኮር እና ሰዎችን ማዕከል ሊያደርግ ይገባል ሲልም አትቷል።
|
አቶ ብሩክ መኮንን የተሰሩት ጥናቶች የተባበሩት መንግሥታት ተልዕኮዎች ከሰላም ማስከበር የዘለለ ሚና እንዲኖራቸው የታቀዱ ናቸው ሲሉ ይናገራሉ።
|
ሽብር እና ድንበር ተሻጋሪ የተደራጀ ወንጀል በሰላም ማስፈን ተልዕኮ ላይ መሰረታዊ ለውጥ አምጥተዋል።
|
የባለሙያዎቹ ጥቆማ እነዚህን ለመቀልበስ ሰላም ማስከበር በቀጥታ ጥቅም ላይ ሊውል አይገባም የሚል ኃሳብ አቅርቧል።
|
ነገር ግን ተፅዕኖ እስካለው ድረስ አንድ ተልዕኮ ቸል ሊለው ይገባል ብዬ አላምንም።
|
በዚያ የአፍሪቃ ኅብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ሰላም አስከባሪ አለ።
|
የተደራጀ ወንጀል ተቃዋሚዎችን እና አል ሸባብን ወደ ወደ ፊት እየገፋቸው ነው።
|
መንግሥት ይኸን ለመፍታት ደካማ በመሆኑ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ መፍትሔ ካልፈለገለት ማን ሊፈታው ነው
|
ከዚህ በተጨማሪ ግጭት ከተከሰተ በኋላ ከመታገል ይልቅ ከመከሰቱ በፊት እንዴት መከላከል ይቻላል የሚለው ኹነኛ መፍትሔ ይሻል።
|
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰላም ማስከበር ተልዕኮን ለማሻሻል ጠንካራ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ሪያና ፓኔራስ ተናግረዋል።
|
አምባሳደሯ የወጪ ቅነሳውን እንደ ታላቅ ስኬት ቢቆጥሩትም ተንታኞች ግን የሰላም ማስከበር ተልዕኮ መፃኢ ፈተና ጠቋሚ ምልክት አድርገውታል።
|
ይሁንና ሐላፊዋ አክለዉ እንዳሉት ወባ አሁንም ከዓለም በርካታ ሕዝብ ከሚገድሉ አምስት በሽታዎች አንዱ ነዉ።
|
በዚሕም ሰበብ የዘንድሮዉ የፀረ ወባ ቀን አብይ መርሕ በጣሙን የአፍሪቃ ሕፃናትን የሚፈጀዉን በሽታ ለመከላከል የሚደረገዉ ጥረት እንዲጠናከር የሚጠይቅ ነዉ።
|
በኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚንስቴር የወባ መከላከያ ዘርፍ አስተባባሪ ወይዘሪት ሕይወት ሰለሞን እንዳስታወቁት የፀረ ወባ ዕለት ኢትዮጵያ ዉስጥም ተከብሮ ነዉ የዋለዉ።
|
ከከሟቾቹ ከአምስት መቶ ሥልሳ ሺሕ የሚበልጡት ጨቅላ ሕፃናት ነበሩ።
|
የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቬዥንና የኦሮሞ ሚድያ ኔትዎርክ ለነዚህ ተከሳሾች እንደ ልሳን አገልግለዋል ሲል የክስ ዝርዝሩ ይጠቅሳል።
|
ዶክተር መረራ ከኅዳር ቀን ዓ ም ጀምሮ እስር ላይ ይገኛሉ።
|
ሦስቱም ተጠርጣሪዎች ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ስረዓቱን በኃይል እንናስወግዳለን በማለት እንደተንቀሳቀሱ የወንጀል ዝርዝሩ ያመለክታል።
|
ዶክተር መረራ በማዕከላዊ እስር ላይ እንደሚገኙ የሚናገሩት ጠበቃቸዉ አቶ ወንድሙ ኢብሳ ደንበኛቸዉ በወንጀል መቅጫ መከሰሳቸዉ ይናገራሉ።
|
እሳቸዉ በሚመሩት ድርጅት ላይ የቀረበዉን ዉንጀላም መሰረተ ቢስ ክስ መሆኑን ይናገራሉ።
|
ስርዓቱ የኔን ስም ተጠቅሞ ዶክተር መረራን ለመጉዳት ያሰበበት ክስ ነዉ የሚሉት ደግሞ ሦስተኛ ተከሳሽ አቶ ጀዋር መሃመድ ናቸዉ።
|
አቶ ጀዋር በአምስተኛ ደረጃ ላይ ክስ የተመሰረተበት የኦሮሞ ሚድያ ኔትዎርክ ሥራ አስኪያጅም ናቸዉ።
|
የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ ግዜያት ሲወነጅለን ነበር የሚሉት አቶ ጃዋር የሚመሩትን ተቋም ከክሱ ነፃ መሆኑን ይናገራሉ።
|
ዶክተር መረራ እስከ ትላንትና ድረስ ክስ ሳይመሰረትባቸዉ ለ ቀናት በእስር እንደቆዩ ጠበቃቸዉ አቶ ወንድሙ ኢብሳ ገልጸዋል።
|
ትላንትና የዋስትና መብት እንዲጠበቅላቸዉ ስምንት ሰዓት ላይ ቀጠሮ ነበራቸዉ።
|
የኢትዮጵያ የግድግዳ ጡፍ መግቢያ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ኢትዮጵያ የቤተሰብ የበዓል አከባበር ሦስት ኢድ አልፈጥሮችን በሦስት የተለያዩ እስር ቤቶች አሳልፏል።
|
ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ጋዜጠኛ ኻሊድ ቤት ጎራ ብሎ የበዓል አከባበሩን ተመልክቷል።
|
የዜናነህ መኮንን የጤና መቃወስ ዜናነህ መኮንን ከ ዓ ም ጀምሮ ከጋዜጠኝነት በተለይም የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ዘዴዎችን ተለይቶ አያውቅም።
|
መጀመሪያ በኢትዮጵያ ራዲዮ ቀጥሎ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና በራዲዮ በዝግጅቶች እና በዜና አቅራቢነት ለረጅም ጊዜ ያገለገለ አንጋፋ ጋዜጠኛ ነው።
|
ወደ እስራኤል ከተሰደደ በኋላም በተለያዩ የራዲዮ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች እና በኢንተርኔት የተለያዩ ዝግጅቶችን በማቅረብ ይታወቃል።
|
በኢየሩሳሌም የዶይቸ ቬለ ተባባሪ ዘጋቢ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ የመካከለኛው ምሥራቅን የፖለቲካ ዲፕሎማሲን ውጥንቅጥን በመዘገብ እና በመተንተን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል።
|
ዜናነህ ከጋዜጠኝነቱ በተጨማሪ የሁለት መጽሐፍት እና የግጥሞች ደራሲ ነዉ።
|
ነጻነት የተሰኘው የበኩር ስራው በጣሊያን የአምስት ዓመት የወረራ ወቅት የነበረውን ጦርነት የሚያሳይ ታሪካዊ ልቦለድ ነው።
|
በሁለተኛ መጽሐፉ ከጣራው ስር ደግሞ የአዲስ አበባን ድብቅ የማህበራዊ ህይወት በልቦለድ ከሽኖ አቅርቧል።
|
ጋዜጠኛው ከጎርጎሮሳዊው ጀምሮ የዶይቸ ቬለ የአማርኛው ክፍል የጣቢያ መክፈቻ እና በዝግጅቶች መግቢያነት የሚጠቀምባቸው ማስተዋወቂያዎች አንባቢም ነዉ።
|
እውቁ ጋዜጠኛ ከጥቂት ወራት በፊት የገጠመው የኩላሊት ሕመም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቷል።
|
ዜናነህ ሁለቱም ኩላሊቶቹ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን ሐኪሞቹ የነገሩት ከጥቂት ወራት በፊት ነበር።
|
ከኩላሊቶቹ ቢያንስ አንዱ በንቅለ ተከላ ካልተቀየረ የጤንነት ሁኔታው አሁን ካለበትም ሊከፋ እንደሚችልም አስጠንቅቀውታል።
|
ስለ ጋዜጠኝነት ህይወቱ ስለ መጽሐፍቶቹ የህዝቡን እርዳታ ስለጠየቀበት የኩላሊት ህመሙ አውግቶናል።
|
የኢትዮጵያውያን ውይይት በፓሪሱ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በፈረንሳይ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር በተካሄደ ውይይት ጥሪውን ያስተላለፈው ኤምባሲው ዜጎችን ለማገልገል ዝግጁ መሆኑንን አስታውቋል።
|
ፈረንሳይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ዘርፎች ሀገራቸውን ሊያግዙ እንደሚገባ ተጠየቀ።
|
ቡድኑ ወደኢትዮጵያ የገባው በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋባዥነት ሲሆን በዚህ አጋጣሚም ህክምና አከናውኗል።
|
ቡና ፈላጊዉ ዓለም በተለይ በተፈጥሮ መንገድ ለሚያድገዉ የጫካ ቡና የሰጠዉ ትኩረት የኢትዮጵያን ደን ከዉድመት ይታደገዉ ይሆን
|
በዓለማችን የጫካ ወይም ወፍ ዘራሽ ቡናን የሚያመርቱ ሃገራት ሶስት ብቻ ናቸዉ።
|
ከእነዚህ ሃገራት አንዷ ደግሞ በሀገር በቀል የተፈጥሮ ደን ዉስጥ ይህን ቡናዋን በማብቀል ትታወቃለች።
|
ይህችዉም ቡናን በዉድ ዋጋ ለጠጪዎች ማቅረቡን የሚያዉቅበት ዓለም በኩራት ጠቀም ባለ ገንዘብ የሚቸበችበዉ አረቢካ የተሰኘዉ ቡና መገኛ ምድር ኢትዮጵያ ናት።
|
በመቶ የሚሆነዉ የተፈጥሮ ደን በእርሻ ሥራ ማስፋፊያ በሰዎች መኖሪያና በሰፈራ እንቅስቃሴዎች እንዳልነበር ሆኗል።
|
በአሁኑ ወቅት ካለዉ የደን ሀብት በመቶዉ የሚገኘዉ በኦሮሚያ መስተዳድና አካባቢዉ ነዉ።
|
ጄፍሪ ያነጋገራቸዉ የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ተቋም አማካሪ እንደሚሉት አማራጭ አጥቶ እንጂ ሕብረተሰቡ የደን ሀብቱን በመንከባከብ ሊያገኝ የሚችለዉን ጥቅም አልዘነጋዉም።
|
ቡናዉ በዓለም ገበያ እዉቅና አግኝቶለት ኑሮዉን የሚያሻሽልበት አማራጭ ሲቀርብለት መተባበሩም ይህንኑ አመላካች ነዉ።
|
ይህም ገበሬዎቹ ለዓለም ገበያ ለሚያቀርቡት ቡና ጥራት ትልቅ ዋስትና ነዉ።
|
እንደዘገባዉ ጃፓኖች በፈጣን ባቡሮቻቸዉ ለሚጓዙ መንገደኞች ይህንን ከጅማ ዞን የተፈጥሮ ደን ዉስጥ የበቀለ ቡና ማቅረብ ከጀመሩ አራት ወራት ተቆጥረዋል።
|
በዓለም ገበያ እጅግ ተፈላጊ የሆነዉ ወፍ ዘራሹ የጫካ ቡና ህልዉና እንዲቀጥልም የተፈጥሮ ደኑን መጠበቁ አማራጭ እንደሌለዉ ነዉ ግልፅ የሆነዉ።
|
ሆኖም ከሽያጩ ያገኙት ከበፊቱ የተሻለ ገቢ ትርጉም ሳይኖረዉ የቀረ አይመስም።
|
ምንም እንኳን አንዳንዶቹ አሁንም ያገኙት ገቢ የእነሱን ወገብ በጣሽ ልፋትና የፈሰሰ ላብ እንደማያካክስ በግልፅ ቢናገሩም።
|
በዚህ መልኩ እንቅስቃሴዉ ተጠናክሮ የኢትዮጵያ የጫካ ቡና ልዩ ሆኖ በዓለም ገበያ ሲቀርብም ደንን ከመራቆት መታደግ መቻሉም ትልቅ ግምት ይሰጠዋል።
|
ማብራሪያ በመስጠት የተባበሩንን የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አራርሳ ረጋሳን ከልብ እናመሰግናለን።
|
የደመራ በዓል አከባበር በጀርመን እንደ ብዙዎች ግምት በዚህ ክብረ በዓል ከ በላይ ሰዉ ነበር የተገኘዉ።
|
በዚህ ዝግጅታችን በፍራንክፈርት እጅግ በርካታ ኢትዮጵያዉያን የተገኙበትን የደመራ በዓል ቃኝተን በአሁኑ ወቅት በአዉሮጳ ብሎም በጀርመን ስላለዉ የስደተኝነት ቀዉስ እናያለን።
|
በየዓመቱም የከተማዉ ከንቲባ አልያም ሌሎች ከፍተኛ የጀርመን ባለስልጣናት በክብር እንግድነት ይጋበዙበታል።
|
ዘንድሮ የፍራንክፈርቱ ደመራ በዓል ላይ በክብር እንግድነት የተጋበዙት አዲስ ተሾመዉ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጀነራል ምህረትዓብ ሙሉጌታም ነበሩ።
|
ከቀኑ አስር ተኩል ሲሆን ምዕመናኑ ትልቁን ደመራ ከበዉ ዘማሪዎች ልብሳቸዉን ለብሰዉ ደመራዉ በተደመረበት ሰፊ ሜዳ ላይ ተሰበሰቡ።
|
ክብረ በዓሉም በፍራንክፈርት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን አስተዳዳሪ በአባ ኃይለመለኮት ተስፋ ማርያም በይፋ ተጀመረ።
|
በፍራንክፈርት ደግሞ በየዓመቱ እንደዚሁ ከ ዓመት ጀምሮ በታላቅ ነዉ የሚከበረዉ።
|
በመጀመርያዎቹ ዓመታት የጀርመን ከፍተኛ ባለስልጣናት የፍራንክፈርት ከተማ ምክት ከንቲባ እየመጣ አብሮን አክብሮአል።
|
የደመራዉም አከባበር ልክ እንደ ሀገራችን ነዉ ደስ ይላል ሕዝቡም ደስተኛ ነዉ።
|
በአባ ኃይለ መለኮት በጀርመን ብሎም በአዉሮጳ የወቅቱ ያለዉን የስደት ቀዉስ በተመለከተ ቤተ ክርስትያኒቱ ምዕመኑ ሁሉ ስለ ችግሩ እንደሚያስብ እንደሚፀልይ ተናግረዋል።
|
ሁላችንም አይተናል ሰምተናል በተለይ በመካከለኛዉ ምሥራቅ ያለዉ ችግር በሶርያ በአፍጋኒስታን በኤርትራ እንደዚሁ ከባድ የስደት መከራ ነዉ ያለዉ።
|
ጀርመኖችም ሁኔታዉ የሁለተኛዉን ዓለም ጦርነት ያስታዉሳል ነዉ የሚሉት በቤተ ክርስትያናችን እንፀልያለን።
|
በአሁኑ ጊዜም ከአዉሮጳ ሀገራት በበለጠ ስደተኞችን የምትቀበለዉ ጀርመን ናት።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.