input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ባን ጊ ሙን ግልፅ እንዳደረጉትም አሁንም የሴቶችን መብት ከማስከበር አኳያ የተሠሩ ሥራዎች ቢኖሩም የሚቀሩት በርካታ ናቸዉ።
|
ከምንም በላይ የሰዎች አመለካከት መሠረታዊ ለዉጥ እንደሚያሻዉም ዋና ፀሐፊዉ ሳያስቡ አላለፉም።
|
በወቅቱም መንግሥታት የሴቶች መብት እንዲከበር የሚደነግገዉን ሕግ ተስማምተዉበት ተቀብለዋል።
|
ለዚህም ዓለም ይህን በይደር ያስቀመጠዉን የቤት ሥራ ትርጉም ባለዉ መልኩ እንዲያጠናቅቅ አሳስበዋል።
|
ዕለቱን አስመልክቶ የወጣ አንድ ጥናት የቤጂንጉን ዉል ከፈረሙት ሃገራት ቱ በሕገ መንግሥታቸዉ ማካተታቸዉን ያመለክታል።
|
ሕጉን በሕግነት መቀበሉ ብቻ በቂ አይደለምና አሁንም እዉን አድርጉት የሚል ጥሪ ነዉ የቀረበላቸዉ።
|
ሕጉን ከተቀበሉ ሃገራት አንዷ ኢትዮጵያ ለተግባራዊነቱ ምን ያህል ተሳክቶላታል
|
የኢትዮጵያ ሴት ማኅበራት ጥምረት ሥራ አስኪያጅ ወ ሮ ሳባ ገብረ መድህን ያስረዳሉ።
|
ቦኮሃራም በሕዝብ ላይ በሚፈፅመዉ አሳዛኝ ድርጊት ወጣት ልጃገረዶችን ከትምህርት ቤት ማገት መንደሮችን ማቃጠል ማኅበረሰቡን ሁሉ ማሸበር እና መግደል በጣም ተጨንቀናል።
|
በአንድ አካባቢ የነበረዉ ቡድን አሁን ወደምዕራብ አፍሪቃና ማዕከላዊ አፍሪቃ ሲስፋፋ እያየን ነዉ።
|
በያዝነዉ ሳምንት መጀመሪያ ነዉ የአፍሪቃ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዝደንት ንኮሳንዛና ድላሚኒ ዙማ የጉባኤዉን ዋነኛ መነጋገሪያ አጀንዳ በዚህ መልኩ ግልፅ ያደረጉት።
|
የአፍሪቃ ኅብረት ሰሜን ናይጀሪያ ዉስጥ በሚንቀሳቀሰዉ ፅንፈኛ እስላማዊ ቡድን ቦኮሃራም ላይ ወታደራዊ ርምጃ ለመዉሰድ አልሟል።
|
ይህም ባለፈዉ መስከረም ወር ናይሮቢ ላይ የመንግስት ባለስልጣናት ፅንፈኛ እስላማዊ የሽብር ድርጅቶችን ለመዋጋት ልዩ ስለበጀት የተነጋገሩበት ዝግጅት አካል ነዉ።
|
እንዲህ ያለዉ ዘመቻ ሲታሰብ የናይጀሪያን ፍላጎት ማካተት እንዳለበት የፀጥታ ጥናት ተቋም የፖለቲካ ተንታኝ ዶክተር ሰሎምን ደርሶ ያሳስባሉ።
|
ናይጀሪያ እንዲህ ያለ ወታደራዊ ዘመቻ በግዛቷ እንደማትፈልግና ቦኮሃራምን ራሷ እንደምትቋቋም ገልጻለች።
|
እንዲህ ያለዉ የፖለቲካዊ መዕክት ነዉ በተደጋጋሚ ከናይጀሪያ ሲነገር የተደመጠዉ።
|
ስለዚህ ናይጀሪያ የዓለም አቀፍ ወታደራዊ ኃይልም ሆነ የፈረንሳይን ጦር ግዛቷ ዉስጥ እንዲዘምት ትፈቅዳለች ብዬ አልገምትም።
|
ለዓመታት የተነገረለት እንዲህ ባለዉ ወቅት ፈጥኖ የሚሠማራ የአፍሪቃ ተጠባባቂ ኃይል በምህፃሩ ን የመገንባቱ ነገር እስካሁን እዉን አልሆነም።
|
የተስፋፋዉ የቦኮሃራም ጥቃት የተናጠል ግብረ ሐይል መመሥረት አጠቃላዩ ትልቅ ሐይል ጋር ሊቀናጅ አይችልም።
|
ይልቁንም የሚያስፈልገዉ ፈጥኖ እርምጃ መዉስድ የሚችልበትን ሥልት መፈለግ ነዉ።
|
የአፍሪቃ ኅብረት በሰላምና ፀጥታዉ ምክር ቤቱ ሥር ይህን ሐይል ማቋቋምና ማዝመቱ ይሳካል ወይ የሚለዉን መገመት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል።
|
ሌላዉ ኅብረቱ በዚህ ጉባኤዉ የሚመለከተዉ በደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች መካከል የቀጠለዉን ግጭትና ዉዝግብ ነዉ።
|
በሌላ በኩል ያለዉ መልካን ዜና የአፍሪቃ የኤኮኖሚ ኮሚሽን በኤቦላ ወረርሽኝ በአህጉሪቱ ኤኮኖሚ ላይ ያደረሰዉ ተፅዕኖ መጠነኛ መሆኑ መገለፁ ነዉ።
|
ድርድር ጦርነት ጦርነት ድርድር ሶሪያ አረብ የቋንቋ ባሕል እምነቱን አንድነት ደፍልቆ መጠፋፊያዉ ካደረገዉ ዘመናት አስቆጥሯል።
|
የሥልክና የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሮሮ ካገልግሎት መስጪያ ዉጪ የደወሉት ቁጥር ከአግልግሎት መስጪያ ክልል ዉጪ ነዉ።
|
ያንኑ ቁጥር ደግመዉ ይሞክሩ መጀመሪያ ከሰሙት የተለየ መልዕክት ይሰማሉ እዚያዉ ኢትዮጵያ፥
|
የጦር ወንጀል በየመን ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ኢህአዴግ እና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከመካከላቸው በሚመርጧቸው አባላት እንዲመራ የተስማሙበት ድርድር እና ፋይዳው የዛሬው እንወያይ ትኩረት ነው።
|
አውሮጳ ጀርመን የሽታይንማየር የአፍሪቃ ህብረት ጉብኝት የህብረቱ ቃል አቀባይ ለ እንደተናገሩት ሽታይንማየር የጀርመንን እና የአፍሪቃ ህብረትን ትብብር የማሳደግ ፍላጎት አላቸው።
|
የጀርመን መንግሥት በአፍሪቃ ህብረት አማካይነት የአባል ሀገራት ልማትን ሊያፋጥኑ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ እየሰራ መሆኑንም ቃል አቀባይዋ ተናግረዋል።
|
የሽታይንማየር የአፍሪቃ ህብረት ጉብኝት የጀርመን ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር በኢትዮጵያ ያደረጉትን የ ቀናት ጉብኝታቸውን ዛሬ አጠናቀው ወደ ጀርመን እየተመለሱ ነው።
|
ፕሬዝዳንቱ ዛሬ እኩለ ቀን ላይ ከአዲስ አበባ ለመነሳት ቢያቅዱም አውሮፕላናቸው ባጋጠው የቴክኒክ ችግር ምክንያት ጉዞአቸው እንዲዘገይ መደረጉ ተዘግቧል።
|
ሽታይንማየር ዛሬ ጠዋት በአፍሪቃ ህብረት ኮሚሽን በመገኘት ከህብረቱ ባለሥልጣናት እና ሠራተኞች ጋር የሀሳብ ልውውጥ አድርገዋል።
|
የህብረቱ ቃል አቀባይ ለ እንደተናገሩት ሽታይንማየር የጀርመንን እና የአፍሪቃ ህብረትን ትብብር የማሳደግ ፍላጎት አላቸው።
|
ያነጋገራቸው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል።
|
የኢትዮ ኤርትራ ጣጣ ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
የአውሮፓ ህብረትና ስደተኞች መግቢያ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ኢትዮጵያ ጠሪያቸው ግልጽ ያልሆነው የኦሮሚያ ሰልፎች ባለፈው ሳምንት በኦሮሚያ ክልል ተከታታይ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሄደዋል፡፡
|
የኦሮሚያ ክልል መንግስት የክልሉ ነዋሪዎች በሰልፎቹ ላይ ከመሳተፍ እንዲቆጠቡ አሳስቧል፡፡
|
የሚለው እያነጋገረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ዛሬም በሱልልታ ተመሳሳይ ተቃውሞ ተካሂዷል፡፡
|
በሱሉልታ ዛሬ የተቃውሞ ሰልፍ ተደርጓል በአዲስ አበባ አቅራቢያ የምትገኘው ሱሉልታ ከተማ ሳምንታዊ የገበያ ቀኗ ሀሙስ ነው፡፡
|
በሳምንቱ መጀመሪያ ሰኞ እና ቅዳሜ ደግሞ አነስ ያሉ ገበያዎችን ታስተናግዳለች፡፡
|
ሱቆቿ ተዘግተው የታክሲ አገልግሎት ቆሞ በከተማዋ ዋና አውራ ጎዳና ለሰዓታት የተካሄደውን የተቃውሞ ሰልፍ ትንፋሿን ሰብስባ ስትከታተል ነበር፡፡
|
ሁኔታው ያስፈራቸው ዕለታዊ ክንውናቸውን ትተው በመኖሪያቸው ሁነው ተቃውሞውን ይከታተሉ እንደነበር ይናገራሉ፡፡
|
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሱሉልታ ነዋሪ ዛሬ ረፋዱን በከተማይቱ የነበረውን ሁኔታ እንዲህ ይገልጹታል፡፡
|
ምን እንደሚሉ አላውቅም ኮኮብ የሌለበት ባንዲራ ይዘው ነው የወጡት ይላሉ፡፡
|
እኚህ ነዋሪ ሰልፈኞቹ ሱቅ ሲያዘጉ መመልከታቸውን እና የታክሲ አገልግሎትም ተቃውሞውን ተከትሎ በከተማይቱ ማቋረጡን ያስረዳሉ፡፡
|
ተቃውሞ እንደሚካሄድ ቀድመው የሰሙት ነገር እንዳልነበር የሚናገሩት ነዋሪው በሰልፉ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ የነበራቸውን ጉዞ ሰርዝው ወደቤታቸው ለመመለስ መገደዳቸውን ይናገራሉ፡፡
|
ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው ሌሎች የከተማዋ ነዋሪዎችም ሰልፍ እንደሚካሄድ መረጃው እንዳልነበራቸው ገልጸውልናል፡፡
|
በጠዋት ወደ ገበያ መውጣታቸውን የሚናገሩ አንዲት የከተማዋ ነዋሪ ተቃውሞው የጀመረው በጋሪ ነጂዎች እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡
|
ጋሪ ነጂዎቹ ተቃውሟቸውን እያሰሙ ወደ ካጂማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከሄዱ በኋላ ተማሪዎች እንደተቀሏቀሏቸው ያብራራሉ፡፡
|
ከዚያ በኋላ የሰልፈኞቹ ቁጥር እያደገ የከተማው ሌላ ነዋሪም አብሯቸው መቃወም እንደቀጠለ ይናገራሉ፡፡
|
ሰላማዊ ነበር ባሉት በዚህ ተቃውሞ ፖሊሶች ሰልፈኞች ከመጠበቅ ውጭ ምንም ዓይነት እርምጃ አልወሰዱም ይላሉ፡፡
|
ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ሌላ የከተማዋ ነዋሪም ተመሳሳይ ገለጻ አላቸው፡፡
|
ሰልፉ ከሶስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ስምንት ሰዓት ድረስ መቆየቱን ይናገራሉ፡፡
|
እጃቸውን ከጭንቅላታቸው በላይ በማጣመር ተቃውሟቸውን ሲገልጹ የነበሩ ሰልፈኞች ያሰሟቸው የነበሩትን መፈክሮች ይዘረዝራሉ፡፡
|
አገዛዙ በቃን የታሰሩት ይፈቱልን ነጻነታችን ይከበርልን አይነት ነው የተላለፈው መልዕክት፡፡
|
በዚሁ አጋጣሚ ከሶማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን የብሩን በመጠን ባላውቅም ብዙ ብር እርዳታ ተሰብስቧል፡፡
|
በሰልፉ ላይ ለኦሮሚያ ክልል አስተዳደር እና ለክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ ድጋፎች ሲደመጡ እንደነበር ገልጸዋል፡፡
|
ከሶማሌ ክልል የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆችን አልረዳም በሚልም የፌደራል መንግስት ላይ ወቀሳ መሰንዘሩን ጠቁመዋል፡፡
|
በሰልፉ ላይ ድጋፍ እና ተቃውሞ ቢስተናገድም ሰልፉን ማን እንደጠራው እንደማይታወቅ ይናገራሉ፡፡
|
እንደውም ከትላንት ጀምሮ አትውጡ ማንም አልጠራችሁም እየተባለ ነው የወጡት፡፡
|
ብዙ ሰው ነው የወጣው ይላሉ የሰልፉን ተሳታፊ ብዛት ሲያስረዱ፡፡
|
ሱልልታ ከዘጠኝ ሰዓት በኋላ ወደ ተረጋጋ ሁኔታ መመለሷን ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡
|
በኦሮሚያ አሁን በተከታታይ እየተካሄዱ ላሉ ተቃውሞች መነሻ በነበረችው አምቦም ባለፈው ረቡዕ የሆነው ተመሳሳዩ ነበር፡፡
|
በሰላም የተጠናቀቀው ይህ ሰልፍ ዱብ እዳ እንደነበር ስሙን መጥቀስ ያልፈለገ አንድ የአምቦ ነዋሪ ለዶይቼ ቬለ ተናግሯል፡፡
|
እንደ አምቦ ሁሉ በዚያው ቀን ጥቅምት ቀን ዓ ም ሻሸመኔ እና ዶዶላ ላይም ሰላማዊ ሰልፎች ተደርገዋል፡፡
|
ለእንዲህ አይነት ሰልፎች ድጋፍ በመስጠት የሚታወቁ መቀመጫቸውን በውጭ ሀገር ያደረጉ ተሟጋቾች እየተካሄዱ ያሉ ሰልፎችን ድጋፍ ነፍገዋል፡፡
|
በኖርዌይ የሚኖረው ግርማ ጉተማ ከኦሮሞ መብት ተከራካሪዎች አንዱ ነው፡፡
|
የአሁኖቹ ግን የተቀናጁ አይደሉም ሁለተኛ ደግሞ ሻሸመኔ ላይ የተከሰተው አሁን በጣም አሳዛኝ ነገር ነው፡፡
|
ሻሸመኔ ላይ ሰልፈኛውን እየመሩ ወደ ወታደር ካምፕ ላይ የሚወስዱ ሰዎች ነበሩ፡፡
|
ያንን ከሰማን ካጣራን በኋላ ነው በነገርህ ላይ እንዲህ እንደድሮው ለመብት ጥየቃ እንዳልሆነ እና የሆነ አካል እንደጠለፈው ዓይነት መረጃ የደረሰን፡፡
|
እና የእኛን ቄሮዎች በፊት ሪፖርት የሚያደርጉልንን የተወሰኑትን ጠልፈውብን ነበር፡፡
|
ሰዎቹ መረጃ ይሰጡናል ማለት ነው ከዚያ በግልጽ በመላው ኦሮሚያ ይካሄዳል ተብሎ ነበር የምንጀምር የነበረው፡፡
|
ስናየው ነገሩ ጥሩ እንዳልሆነ እና ወጣቱ ከእንደዚህ አይነት ነገር እንዲቆጠብ ነግረናል ፡፡
|
በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡን የኦሮሚያ መንግስት የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋን ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም፡፡
|
ማህበራዊ ድረ ገጾች እና ሀሳብን በነጻ መግለፅ ማህበራዊ ድረ ገጾች ሰዎች የግል ሀሳባቸውን በነጻ እንዲገልጹ እንዲወያዩ እና እንዲከራከሩ እድል ፈጥረዋል።
|
የተለያዩ የማህበራዊ ድረገጾች ከሌሎች ሰዎች ጋር በዓለም ዙሪያ ሀሳብን ለመለዋወጥ ከፍተኛ እድል ፈጥረዋል።
|
አዳዲስ መረጃዎችን በጥቂት ሰከንድ ውስጥ ማግኘት እና የግል ሀሳብን ለሌሎች ማካፈል ይቻላል።
|
መረጃ ሰጪ እና አስተማሪ መልዕክቶች የሚያስተላልፉ እንዳሉ ሁሉ የዛኑ ያህል ህዝብን የሚያደናግሩ እና የሚያሳስቱ የጥላቻ አስተሳሰቦችን የሚያሰራጩ መልዕክቶችንም የሚፅፉ አሉ።
|
በተለይ ኢትዮጵያን የሚመለከቱ መረጃዎችን በተደራጀ መልኩ መልሰው ለኢትዮጵያውያን ከሚያቀርቡ ድረ ገዶች አንዱ ድሬ ቱዩብ ነው።
|
ድሬ ቲዮብ የፌስ ቡክ ገፁ ላይ ብቻ ሚሊዮን የሚጠጉ ተከታዮች አሉት።
|
የድሬ ቲዮብ መስራች እና ባለቤት ቢኒያም ነገሱ የኢትዮጵያውያንን ማህበራዊ ድረ ገጽ አጠቃቀም ለማጤን በቂ እድል አግኝቷል።
|
ዶይቸ ቬለም በተለየያዩ ቋንቋዎች ባሰናዳቸው የፌስ ቡክ ገጹቹ መረጃዎችን ለተጠቃሚዎቹ ያቀርባል ያወያያልም።
|
ባልደረባዬ እሸቴ በቀለ የገጹን ተጠቃሚዎች እያወያየ አስተያየታቸውንም ሰብሰብ አድርጎ ያቀርባል።
|
እሱስ የኢትዮጵያውያን የማህበራዊ ድረ ገፅ አጠቃቀምን በተለይ የዶይቸ ቬለ ገፅን ተጠቃሚዎች እንዴት ይገልጸዋል
|
ኢትዮጵያ የሐዋሳ የዛሬ ውሎ ግጭትም እንደነበር የዓይን እማኞች ተናግረዋል።
|
የሃዋሳ የዛሬ ውሎ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ርዕሰ ከተማ ሃዋሳ ዛሬ ውጥረት ሰፍኖ ነው የዋለው።
|
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተነገረ በኋላ በነቀምቴ እና በደምቢዶሎ ስለነበረው ተቃውሞ እና የጸጥታ ኃይላት ርምጃም አስተያየቶችን አሰባስበናል።
|
የምክር ቤት አባላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን እንዳያጸድቊ ስለነበረው ውትወታም የተጻፉትን እናካትታለን።
|
ዋካንዳ ሰሞኑን በዓለም ዙሪያ የበርካቶች መነጋገሪያ የኾነው ብላክ ፓንተር የተሰኘው የሆሊውድ ፊልም ታሪክ የሚፈጸምባት ከተማ ናት።
|
ከዋካንዳ በተለየ መልኩ ግን ኢትዮጵያ ነጻነቷን ጠብቃ የቆየችው በአስማታዊ ንጥረ ነገር ሳይኾን በጀግኖች ተጋድሎ ነው ይላል ጽሑፉ።
|
ኢትዮጵያ በቀድሞ አጠራሯ አቢሲኒያ በመካከለኛው ክፍለ ዘመን ለአውሮጳውያን ምሥጢር የነበረች መኾኗ ከዋካንዳ ጋር በመጠኑ ያመሳስላታል ሲልም አክሏል።
|
በ ብላክ ፓንተር ፊልም ላይ አብይ ገጸ ባሕሪው ንጉሥ ቲ ቻላ ከንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምንሊክ ጋር እንደሚመሳሰል ደ ብርሀን ገልጧል።
|
ዳግማዊ ዓጼ ምንሊክም የ ዓመት ልጅ ሳሉ በንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ተጠልፈው መወሰዳቸው በአድዋ ድልም ለአፍሪቃውያን ኩራት መኾናቸውን በማነጻጸር ያቀርባል።
|
ደ ብርሀን ከጽሑፉ ጋር አያይዞ ያቀረባቸው የሌሎች ሰዎች የትዊተር መልእክቶችም ተመሳስሎውን የሚያጠናክሩ ናቸው።
|
ኤም ኤንድ ጂ ፍራይዴይ የተባለው የትዊተር ገጽ፦ የዋካንዳ ታሪክ ሊነጻጸር የሚችለው ከኢትዮጵያ ጋር ብቻ ነው ብሏል።
|
እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር አስጥቶ ደሙን ለሀገሩ ፍቅር አፍስሶ ለአፈሩ ክብር አፈር ለብሶ እሱ ወድቆ ሀገሩን የማያቆም እዚህ ያለ እንዳይመስልህ
|
እቴጌ ጣይቱ ብጡል ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ አማኑኤል ተስፋዬ በትዊተር ያሰፈረው ከታሪካዊ ተውኔት የተቀነጨበ ጽሑፍ ነው።
|
ሔዋን ዘ ስምዖን፦ አድዋ የአሜሪካ ድል ቢኾን ኖሮ በሺህ የሚቆጠሩ የተለያዩ አይነት ፊልሞች ይሠሩ እንደነበር ትዊትር ገጽ ላይ ጠቅሳለች።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.