input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ሆኖም ኛ ዓመቱ ሊደፍን እጅግ ጥቂት ቀናት ሲቀሩት በበረዶው ላይ በፍጥነት ይንሸራተትና የራስ ቅሉ ከድንጋይ ጋር ይላተማል።
|
ራሱ ላይ የደፋው መከላከያ ቆብ ተጠርምሶ የራስ ቅሉ በከፍተኛ ደረጃ ይጎዳል።
|
በፍጥነት ሀኪም ቤት ቢወሰድም አደጋው ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ አዕምሮው ውስጥም ጉዳት እንዳስከተለ ሐኪሞች በወቅቱ አስታውቀዋል።
|
ሹማኸር ለረዥም ጊዜያት ሐኪም ቤት ውስጥ ራሱን እንደሳተ ለመቆየት ተገዷል።
|
ሹማኸር ራሱን ማወቁ በሥራ አስኪያጁ በኩል ይፋ የሆነው አደጋ ከተከሰተ ከስድስት ወራት በኋላ ነበር።
|
ስዊትዘርላንድ ጔኔቫ ወሚገኘው ቤቱ ተዛውሮ የሕክምና ክትትል ከጀመረ ሦስት ወራት ተቆጥሯል።
|
ፈርናንዶ ቶሬዝ ከኹለት ቀናት በፊት በሰጠው መግለጫ ከቸልሲ ወደ ጣሊያኑ ኤስ ሚላን በማቅናት በቋሚነት መጫወት እንደሚፈልግ ገልጦ ነበር።
|
ሆኖም ወደ አትሌቲኮ ማድሪድ እንደሚያቀና ቡድኑ በድረ ገፁ ማረጋገጫ ሰጥቷል።
|
ዝውውሩ በውሰት ሲሆን ለአንድ ዓመት የሚቆይ መሆኑም ይፋ ሆኗል።
|
ቶሬዝ በ ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ቸልሲ ከመዛወሩ በፊት ለሊቨርፑል ለ ዓመት ተሰልፎ ተጫውቷል።
|
ወደ ሊቨርፑል ከማቅናቱ በፊት ደግሞ የ ዓመት ልጅ ሳለ የስፔኑ አትሌቲኮ ማድሪድ ማሊያን ለብሶ ተጫውቷል።
|
በወቅቱ ለአትሌቲኮ ማድሪድ ተሰልፎ በ ግጥሚያዎች ግቦችን ከመረብ ማሳረፍ ችሎ ነበር።
|
ፈርናንዶ ቶሬዝ የፊታችን ሰኞ የሐኪም ምርመራውን አጠናቆ ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ልምምድ እንደሚጀምር ቡድኑ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
|
ሊቨርፑል የዌስት ብሮሚቹ አጥቂ የ ዓመቱ ሣይዶ ቤራሂኖ ላይ ዓይኑን ጥሏል።
|
የዌስት ብሮሚቹ አጥቂ ከ ዓመት በታች የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ጊዜ ተሰልፎ ግቦችን ማስቆጠሩ ይታወቃል።
|
ሊቨርፑል ሣይዶን ለማስመጣት ሲሯሯጥ ቀደም ሲል ለቡድናችን ያስፈልገናል ያለለት የባየር ሙይንሽኑ የክንፍ ተጨዋች ዤርዳን ሻቃሪን ፈጣኖች ሊሞጨልፉት ነው።
|
የቀድሞው የሊቨርፑል አሠልጣኝ ዴቪድ ሞየስ በበኩላቸው አሁን ለሚያሠለጥኑት የስፔኑ ሪያል ሶሴዳድ ቡድን የሊቨርፑሉ ኤምሬ ካንን በውሰት ማምጣት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
|
የጣሊያኑ ሣምፕዶሪያ ቡድን የሊቨርፑሉ አጥቂ ማሪዮ ባሎቴሊን ከሰሞኑ መውሰድ እንደሚፈልግ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
|
ከአራት ወራት በፊት በ ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ሊቨርፑል የመጣው ማሪዮ ባሎቴሊ በ ጨዋታዎች ኳስ ከመረብ ያሳረፈው ለኹለት ጊዜ ብቻ ነው።
|
ማሪዮ ባሎቴሊ ቸልሲ የክሮሺያው የፊት አጥቂ አንድሬ ክራማሪችን በሚቀጥለው ወር ወደ ቡድኑ ለማስመጣት ሚሊዮን ፓውንድ መመደቡ ተገልጧል።
|
የጣሊያኑ ኢንተር ሚላን የአርሰናሉ አጥቂ ሉቃስ ፖዶሊስኪን ለመውሰድ መቃረቡ ተነግሯል።
|
ኢንተር ሚላኖች ከትናንት በስትያ ከአርሰናል ዋና ሰዎች ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ጀርመናዊውን የአርሰናል አጥቂ ለመውሰድ ተቃርበናል ብለዋል።
|
አርሰናል በበኩሉ የዌስት ሐሙ ተከላካይ ዊንተን ራይድን ለማስመጣት ሚሊዮን ፓውንድ መመደቡ ታውቋል።
|
በ ነጥብ የአውሮጳ የዓመቱ ምርጥ ስፖርተኛ ተብሎ የተሸለመው በፎርሙላ አንድ የመኪና ሽቅድምድም ባለድሉ እንግሊዛዊው ሌዊስ ሐሚልተን ነው።
|
ሠርቢያዊው የሜዳ ቴኒስ ዝነኛ ኖቫክ ጆኮቪች ክሪስቲያኖ ሮናልዶን በልጦ በ ነጥብ ሦስተኛ ሆኗል።
|
ለሪያል ማድሪድ የሚጫወተው የፖርቹጊዙ አጥቂ ክሪስቲኖ ሮናልዶ ድምፅ ከሰጡት ጋዜጠኞች ያገኘው ነጥብ ሲሆን ደረጃው አራተኛ ነው።
|
ማሪዮ ሌሚና ከ ዓመት በታች የፈረንሣይ ቡድን ውስጥ ተሰልፎ የዓለም ዋንጫ መጨበጡ ይታወቃል።
|
ማሪዮ በፈረንሣይ ዋናው ቡድን ጥሪ ይደረግልኛል በሚል ተድፋ እየተጠባበቀ መሆኑም ታውቋል ።
|
የጋቦን ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዙሪያ ተሰልፈው የሚጫወቱ ድንቅ ተጨዋቾችን ማካተቱ ተገልጧል።
|
ከተጨዋቾቹ መኻከል የቦሩስያ ዶርትሙንዱ አጥቂ ፒየር ኤመሪክ የካርዲፉ ተከላካይ ብሩኖ ማንጋ እና የቻርልተን አትሌቲክ አጥቂ ፍሬድሪክ ቡሎት ይገኙበታል ተብሏል።
|
ምድቡ የአፍሪቃ ዋንጫ አስተናጋጇ ኢኳቶሪያል ጊኒ ቡርኪና ፋሶ እና ኮንጎ ይገኙበታል።
|
በሚል ጥያቄ ሲያስደምሙ ደግሞም ሲያስደንሱ የማታ የማታ ደግሞ በዚያዉ በዉብ የሙዚቃ ድግሳቸዉ ምዕራባዉያኑን ወደ ኢትዮጵያ ሲጋብዙ ሰንብተዋል።
|
አንጋፋዉ ከያኒ አየለ ማሞ በመድረክ ማንዶሊንን ከመጫወት የሙዚቃ ቡድኑን በድምፅ ከማጀብ ባሻገር በዉዝዋዜያቸዉ የእድምተኛዉን ቀልብ ስበዉ ነበር ያመሹት ።
|
በአሁኑ ሰዓት አኩስቲክ ጃዝ ባንድ ወደ አገር ቤት ተመልሶ የሙዚቃ ድግሱን ለማሳየት ወደ ቻይና ለመጓዝ ዝግጅት ላይ እንደሆነም ተነግሮአል።
|
በሙዚቃ ድግሱ ምሽት የተገኘዉ አብዛኛዉ ጀርመናዊ ታዳሚ ኢትዮጵያን በስራ ጉዳይ የሚያዉቅ አልያም ኢትዮጵያዊ ባልንጀራ ያለዉ በመሆኑ ነበር።
|
ለዶቼ ቬለ ራድዮ ጣብያም ትዉስታ የሚለዉን የሙዚቃ አልብሙን ለማስታወሻ ሰትዋል።
|
ችግሩ ያሳሰባቸዉ የተፈጥሮ ሐብት ተሟጋቾችና የሐይቁ ተጠቃሚዎች አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጠዉ በተደጋጋሚ ይጠይቃሉ።
|
የየስምጥ ሸለቆ ሐይቆች ልማት ፅሕፈት ቤት እና የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ለረጅም ጊዜዉ ጥያቄ መልስ ለመስጠት መዘጋጀታቸዉን ይናገራሉ።
|
የሀዋሣ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ተድላ ወ ሚካኤል ከሀዋሣ ሀይቅ ጋር ያላቸው ትውውቅ አራት አስር ዓመታትን ይሻገራል፡፡
|
በወቅቱ የሐይቁ ዳርቻ ጥቅጥቅ ባለደን የተሸፈነ በመሆኑ ሰዎች በቅርበት ካልተጠጉ በቀር እንዳአሁኑ ከርቀት ለማየት ይቸገሩ እንደነበርም ያስታውሳሉ፡፡
|
ይሁን እንጂ የሀይቁን ዙሪያ መለስ የከበበው ደን ለማገዶ መሬቱን ደግሞ ለእርሻ ሥራ በመዋሉ ዛሬ ላይ ያኔ የነበረውን ውበቱን ማጣቱን ይናገራሉ፡፡
|
ከስምጥ ሸለቆ ሀይቆች አንዱ የሆነው የሀዋሣ ሀይቅ ሕገ ወጥ የእርሻ ሥራዎች ከሚካሄድባቸው አካባቢዎች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡
|
ሊቢያ የለዉጥ ጅምር አንደኛ አመት የያኔዉ እስረኛ ያሁኑ ሚንስትር፥
|
መታሰራቸዉን የሰማዉ አምስት መቶ ያሕል የቤንጋዚ ሕዝብ ፖሊስ ጣቢያዉን ከበቦ ይዘመር ፥
|
ግን ለአንድ ሐገር ሕዝባቸዉ የሚያልሙ የሚያደርጉት ያቃረናቸዉ የሥልጣን ሙያ ጠልቅ ልዩነት ያራራቃቸዉ ሁለት ሰዎች።
|
የዚያን ቀን ሲገናኙም የዓላማ ምግባራቸዉ ቅራኔ የማይታረቅነቱን በማወቅና መጪዉን እኩል ባለማሳወቅም አንድ ነበሩ።
|
የስለላዉ የበላይ አብዱላሕ ሴኑሲ ለብዙ ዘመን ብዙ ጊዜ ያደረጉትን መድገማቸዉን እንጂ የመሪያቸዉን ሞት የሥርዓታቸዉን ዉድቀት ማፅደቃቸዉ መሆኑን አላወቁም።
|
ከዚያ በፊት እንደሚያዉቁት የሚደርስባቸዉን ሥቃይ የሚገደሉበትን ዕለት መቼነት እያሰላሰሉ እስር ቤት ተወረወሩ።
|
አርብ የሊቢያ ሕዝባዊ አመፅ አንደኛ አመቱ ተከበረ የአመፁ አንደኛ አመት፥
|
ለዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳት ለባራክ ኦባማ ደግሞ እራሳቸዉ ኦባማ ያኔ እንዳሉት ከመሐመድ ጅብሪል፥
|
ካሁኑ የሊቢያ መሪ ከሙስጠፋ አብዱል ጀሊልም ደስታ አለፍ ያለ ዓይነት ነበር።
|
በዓለም አቀፉ አሸባሪ ድርጅት አል ቃኢዳ ላይ የተቀዳጁት ድል ማጠናከሪያ ነበር።
|
ከሁሉም በላይ ኦባማ እንደተናገሩት የቃዛፊ መገደል መስተዳድራቸዉ የኢራቅና አፍቃኒስታኑን ጦርነት በድል አድራጊነት የማጠናቀቁ ዋቢ አድርገዉት ወይም መስሏቸዉ ነበር።
|
ሁለት ሺሕ አስራ አንድ ዘመኑ በሙሉ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ ፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ ከዋሽንግተን።
|
ይሕ የጋዛፊ መገደል የሆነዉ የአሜሪካ አመራር በመላዉ ዓለም በተጠናከረበት ወቅት ነዉ።
|
አሁን ደግሞ ሊቢያ ዉስጥ ከወዳጆቻችንና አጋሮቻችን ጋር ያከናወነዉ ምግባር በሃያ አንደኛዉ ምዕተ ዓመት የጋራ እርምጃ ሊያከናዉነዉ የሚችለዉን አሳይተናል።
|
ተወላጆች የፖለቲካዉን ሥልጣንም የደለበዉን ሐብትም የአምበሳ ድርሻ ተጋሪ የመሆናቸዉ መሠረት ነዉ።
|
ለአብዛኛዉ ሊቢያ ደግሞ ያኔ ኦባማ እንዳሉት ከረጅም ዘመን አምባገነናዊ አገዛዝ የመላቀቅ ምኞቱ ስኬት፥
|
ዕለቱ ቃዛፊ ያሰቃያቸዉ እና ያጠፋቸዉ ወገኖቻቸዉን የሚያስታውሱበት እና የአዲስ ዘመን ቃል የሚያማትሩበት ነዉ።
|
በርግጥም የሊቢያ ሕዝብ ከዚያ ቀን ለመድረስ ወዶም ሆነ ተገዶ፥
|
አዉቆም ሆነ ሳያዉቅ ስምንት ወር ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ በትንሽ ግምት ከሰላሳ ሺ በላይ ወገኖቹን ሕይወት ለቃዛፊ ጦር ታንክ፥
|
ከሐምሳ ሺሕ የሚበልጡ ወገኖችን አካል የሰወስቱ ወገኖች ቦምብ ሚሳዬል ጥይት አረር ማብረጃ ማድረግ ነበረበት።
|
ቁስለት የዳነዉ ሊቢያዊዉ በቢሊዮን ዶላር የሚገመት የሐብታም ሐገሩ ሐብት ንብረት፥
|
ምጣኔ ሐብታዊ ሥርዓት አስመርሮት የተሻለ ኑሮ ነፃነት ፍለጋ የተሰደደ በሺ የሚቆጠር አፍሪቃዊ የባሕር ዉስጥ አዉሬ ሲሳይ መሆን ነበረበት።
|
የአርባ አንድ ዘመን ሥርዓታቸዉን ለገረሰሰዉ ጦርነት መለኮስ ሰበብ የሆነዉ የቤንጋዚ ሕዝብ ተቃዉሞ ነበር።
|
ተቃዉሞዉ የተጀመረበት አንደኛ አመት ባለፈዉ አርብ ሲከበር አንዲት የቤንጋዚ ወጣት ተማሪ እንዳለችዉ ቢያንስ ቤንጋዚ ብዙ ተቀይራለች።
|
ባለፈዉ አርብ ከዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳት ቢሮ የወጣዉ መግለጫም ፕሬዝዳንቱ ባለፈዉ ጥቅምት ካሉት ጋር አይጣጣምም።
|
በዓለም አቀፉ የሠብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምንስቲ ኢንተርናሽናል የሊቢያ ጉዳይ አጥኚ ካርስተን ዩርገንሰን እንዳሉት ደግሞ ሊቢያ ዛሬም ሥልጣን የያዘ፥
|
ካለፈዉ ጥር አጋማሽ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሊቢያ ነበርን።
|
እኛ ከመድረሳችን ከአንድ ሰዓት በፊት እንኳን የተገረፉ እንደነበሩ ነግረዉናል።
|
በድብደባና ግርፋት ብዛት በየእስር ቤቱ ወዳጅ ዘመዶቻቸዉ የሞቱባቸዉን ሰዎች አነጋግረናል።
|
የእነዚሕ ሰዎች ቤተ ሰቦች እስር ቤት ዉስጥ እንደሚሰቃዩት ሁሉ ፍትሕን ይጠይቃሉ።
|
የመብት ተሟጋቹ ድርጅት አጥኚ ሊቢያ እስር ቤቶች ሥላዩ ሥላጠኑት ከለንደን ሲናገሩ በቀደም አርብ፥
|
የሊቢያዉ የወጣቶች እና የስፖርት ሚንስትር ፈትሒ ተረቤል የአምና ይኼኔ ትዝታ፥
|
የሕግ ባለሙያዉ ከመያዛቸዉ ከሁለት ቀን በፊት የሊቢያ ሕዝብ የኮሎኔል ሙዓመር ቃዛፊ አገዛዝን በመቃወም አደባባይ እንዲወጣ የሚጠይቅ ፅሁፍ በኢንተርኔት አሰራጭተዉ ነበር።
|
በተለይ በዚያ አመት ሐሙስ በሚዉለዉ የካቲት አስራ ሰባት ሕዝቡ የቁጣ ዕለት ብሎ ብሶቱን ባደባባይ እንዲገልፅ ተርቤል ይጠይቃሉ።
|
የካቲት አስራ ሰባት ለቤንጋዚዎች የቆየ በደል የተፈፀበት ዕለትም ነዉ።
|
የሚወነጅሉት ኮሎኔል ሙዓመር ቃዛፊ ከዚያ ጊዜ ጥቂት ቀደም ብሎ ከነ ቡሽ፥
|
ከነ ቤርሎስኪኒ የጀመሩትን ወዳጅነት ለመጠበቅ ሲሉ ሰልፈኛዉ እንዲበተን ያዛሉ።
|
የቤንጋዚ ነዋሪ በተለይም ኢንተርኔት የሚያገኘዉ ወጣት የቱኒዚያ ግብፆችን አመፅ ጀግንነት ዉጤቱንም እየቀላወጠ፥
|
የካቲት አስራ ሰባት ሲጠብቅ ነዉ የሕግ ባለሙያዉን ፅሁፍ ያነበበዉ።
|
መልዕክቱ የቱኒዝ ካይሮ የዘመናት ፖለቲካዊ ሥርዓትን የገለባበጠዉን ሕዝባዊ አብዮት በጥሞና ለሚከታተሉት፥
|
አብዮቱ ድንበር ተሻግሮ ወደ ደቡብ ዝቅ ቢል የሚያከሽፉበትን ሥልት ለሚያብሰለስሉት ለትሪፖሊ ሹማምንት ልዩ ትርጉም ነበረዉ።
|
እና መልዕክቱ እንደበተነ ወደ ቤንጋዚ የገቡት የሰለላዉ ድርጅት የበላይ አብዱላሕ አል ሴኑሲ ፀሐፊዉ እንዲታሰሩ ወሰኑ።
|
የአዲሶቹ የሊቢያ መሪዎች አጋሮች የሴኑሲን የትዕዛዝ ወረቀት የያዙት ነጭ ለባሾች ተርቤልን ከመኪናቸዉ አዉርደዉ ቤንጋዚ ፖሊስ ጣቢያ እስር ቤት ወረወሯቸዉ።
|
የዚያኑ ቀን ማታ ሴኑሲ ተርቤልን አስጠርተዉ ለሁለት ሰአታት ያሕል አነጋገሯቸዉ።
|
አንዳዴ ያስፈራራኝ ሌላ ጊዜ ደግሞ አድቤ እንድቀመጥ ይመክረኝ ነበር።
|
በዚያች ማታ ቤንጋዚ የተጀመረዉ ሕዝባዊ አመፅ የአርባ አንድ ዘመኑ ሥርዓት የፍፃሜ መጀመሪያ መሆኑ አላነጋገረም።
|
ሕዝባዊ አመፅ ግን እንደ ሊቢያ ጎረቤቶች በሕዝብ ፍላጎትና ጥያቄ ተጀመረ እንጂ በሕዝብ ሙሉ ተሳትፎ፥
|
ደም ባራጨ ዉጊያ ጦርነት አዝግሞ በብቀላ ቂም ቁርቁስ ነዉ ያበቃዉ።
|
የአምንስቲ ኢንተርናሽናሉ አጥኚ እንዳሉት ደግሞ የድሕረ ቃዛፊዉ ሥርዓተ አልበኝነት ከእስካሁኑም እንዳይብስ ነዉ ያሁኑ ሥጋት።
|
ችግሩ ደግሞ እነዚሕ ሰዎች እስረኞቹን የሚቆጣጠሩት ሚሊሺያዎች ከሕግ በላይ መሆናቸዉ ነዉ።
|
ያነጋገርናቸዉ ሕግ አስከባሪዎች በግልፅ እንደነገሩን ሚሊሺያዎቹ ማንም የሚቆጣጠራቸዉ የለም።
|
እና አሁን ያለዉ ሥጋት የሊቢያ ሁኔታ ከእስካሁኑም ይበላሻል የሚለዉ ነዉ።
|
የኤርትራ ስደተኞች ዳዳብ የሚገኙ ሶማሊያውያን የሄልሙት ሽሚድት ዜና ዕረፍትና የሃዘን መግለጫ መግቢያ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
የኩላሊት ተግባር መዳከም ምንነት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ብዙዎች ለኩላሊት ህመም ስለመዳረጋቸው በሰፊዉ ሲወራ ይሰማል።
|
ለህክምና ከመድረስ በፊት ኩላሊት ሥራው እንዲዳከም ወይም እንዲቆም የሚያደርገው ምን ይሆን
|
ደምን የማጣራት ብሎም በምግብ ሆነ በመድኃኒት ምክንያት የወደሰዉነት የገቡ መርዛማ ነገሮችን የማስወገድ ታላቅ ኃላፊነት ያለበት የሰውነት አካል ነው ኩላሊት።
|
ቢያንስ እስከአሁን ወደ አራት መቶ የሚጠጉ ሕፃናት ሞተዋል ሌሎች ሁለት ሺህ የሚሆኑ ደግሞ አስቻኳዩ ሕክምና እንደሚያስፈልጋቸው እናውቃለን።
|
በሺዎቹ ለሚቆጠሩት ሕፃናት ሊኖሩበት የሚችሉ ንፁሕ የተፈጥሮ አካባቢ የለም ለማለት ይቻላል ምክንያቱም የሚኖሩባቸው ቤቶች፡ ውሀው፡ በጠቅላላ አካባቢው በእርሳሱ ማዕድን ተበክለዋል።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.