input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ቤተሰቦቻቸውም በማዕድናቱ ውስጥ መሥራታቸውን በመቀጠላቸው መኖሪያ ቤቶቹ ብክለት ሊወገድ አልቻለም።
|
ይሁንና፡ ይላሉ፡ የሂውማን ራይትስ ዎች የጤና ተመራማሪ ወይዘሮ ጄን ኮኸን ይህ ተግባሩ ቀላል አይሆንም።
|
እና ያካባቢው መስተዳድር ችግሩን ውጤታማ እና አጠቃላይ በሆነ መንገድ ለመታገል ቁርጠኝነት እና ከፌዴራሉ መንግሥትም ድጋፍ ያስፈልገዋል።
|
ፌዴራሉ መንግሥት እስካሁን በዚሁ አኳያ ይህ ነው የሚባል ሚና አልተጫወተም።
|
እንዲያውም፡ የፌዴራሉ የማዕድን ሚንስትር ችግሩን ለመታገል በዛምፋራ ፌዴራዊ ክፍለ ሀገር ያሉ ማዕድናት ሁሉ እንዲዘጉ የሚያዝ መግለጫ ትናንት አውጥቶዋል።
|
ይህ ካሁን ቀደም ተሞክሮ ነበር ግን ችግሩን ይበልጡን ነበር ያባባሰው።
|
ይህ ሲሆን ያካባቢው ነዋሪዎች ቤተሰቦቻቸውን አደጋ ላይ ሳይጥሉ በማዕድኑ ሥራ መሥራታቸውን ሊቀጥሉ ይችላሉ።
|
ሦስተኛው፡ ያካባቢው ሕፃናት በእርሳስ ማዕድኑ ብናኝ ተመርዘው መሆን አለመሆናቸውን በምርመራ ማጣራትና ማከም ይሆናል።
|
የፖለቲከኞቹ ተሥፋ እና ሥጋት በአዲስ አመት የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች አዲሱን አመት ሲቀበሉ ተስፋ እና ምኞታቸው እጅጉን የተራራቀ ነው።
|
ጠቅላይ ሚኒሥትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በዋዜማው ባደረጉት ንግግር በአዲሱ አመት መንግሥታቸው የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ እንዲጎለብት ጠንክሮ ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።
|
ጠቅላይ ሚኒሥትር ሐይለማርያም ደሳለኝ እና ኢሕአዴግ አብዝቶ የፈተናቸውን እስከ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ድረስም ያንደረደራቸውን ዓ ም ተሰናበቱ።
|
የኢትዮጵያ መንግሥት በዋዜማው ባዘጋጀው ድግስ ጠቅላይ ሚኒሥትሩ በእርግጥ የጸጥታ መደፍረስ በተጫነው ዓ ም የገጠሟቸውን ፈተናዎች አልጠቀሱም።
|
ጠቅላይ ሚኒሥትሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በታደሙት እና በቀጥታ የቴሌቭዥን ሥርጭት በተላለፈው ንግግራቸው ስለ መቻቻል እና አንድነት ሰብከዋል።
|
ጠቅላይ ሚኒሥትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የመንግሥታቸውን ውጥኖች ከግብ ለማድረስ የአገሪቱ ዜጎች ያልተቆጠበ ያሉትን አስተዋፅዖ እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
|
ሰላማችን እንዲረጋገጥ ሙስና እና ብልሹ አሰራር ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ የጀመርንውን የጸረ ሙስና ትግል አጠናክረን እንቀጥላለን።
|
ዶ ር ያዕቆብ ሐይለማርያም ኢትዮጵያ አዲሱን አመት ስትቀበል እንደ ጠቅላይ ሚኒሥትሩ ተስፈኛ አይደሉም።
|
ብዙም የሚባል ነገር የለም የሚሉት የሕግ ባለሙያ በአሮጌው አመት የተከሰቱ ኩነቶችን እያስታወሱ ይብሰለሰላሉ።
|
የበርካታ ሰዎች ህይወት ያለፉባቸው አካል የጎደለባቸው የቆሼ እና የኢሬቻን የመሰሉ አደጋዎች ኃላፊነት ያለባቸው ወገኖች ተጠያቂ አለመሆናቸውን እያነሱ ይተቻሉ።
|
ጠቅላይ ሚኒሥትሩ የጠቀሱት የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት እንዲህ በቅርበት ለመምጣቱም እርግጠኛ አይደሉም።
|
ደግሞም እንዲህ እንዲያደርግ የሚገፋፋው ሌላ ፓርቲ እስከ ሌለ ድረስ ያ ፓርቲ በጀመረው መስመር ይቀጥላል።
|
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ በበኩላቸው መልካም ምኞት መደርደር ከባድ አልነበረም ሲሉ ይናገራሉ።
|
አገሪቱ ገጥመዋታል የሚሉትን ውስብስብ ችግሮች እየጠቀሱ የኢትዮጵያ መንግሥት ተጨባጭ መፍትሔ ለማበጀቱ ግን እርግጠኛ አይደሉም።
|
ስለ ፍቅር ስለ ሰላም ማውራት የሚቻለው ከአሁን በፊት በግፍ የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞችን ለመፍታት ፈቃደኝነት ቢገኝ ኖሮ ነበር ።
|
ስለዚህ መጪው ዓመት እግዚያብሔር ከፈቀደ እነዚህ ሁሉ የሚስተካከሉ እና ለሕዝባችን ሰላም ፍትኃዊ አንድነት ሁሉ እኛ እንመኛለን።
|
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሙሉጌታ አበበ እንደ አቶ ሙላቱ ሁሉ ያለፈው ዓመት ፈታኝ እንደነር ይስማማሉ።
|
እርሳቸው ያለፈው ዓመት ተቃውሞ የአገሪቱን የፖለቲካ ሥርዓት ለማሻሻል ሁነኛው መንገድ እንደሆነ ያምናሉ።
|
በሚመጣው አመት ቢሆን ጥሩ ነው ብዬ የማስበው ሕዝቡ በሰላማዊ ትግል ሥርዓቱን በካርድ ለመቀየር ንቁ ተሳትፎ እንዲኖረው ነው።
|
ይቺ አገር እንደ አገር እንድትቀጥል ዜጎቿ በዴሞክራሲ መስመር እንዲጓዙ እና ዴሞክራሲ በአገሪቱ እንዲሰፋ ንቁ ተሳትፎ ቢኖረው ጥሩ ነው ብዬ አስባለሁ።
|
አዲስ አበባን በተመለከተ አቋማችን ከጋዜጠኛ እና ከሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ እስክንድር ነጋ ጋር ተመሳሳይ ነው ለማለት ያህል ነው።
|
ማንኛውም የከተማዋ ነዋሪ በህጋዊ መንገድ ለመደራጀት የሚያደርገውን ጥረት እደግፋለሁ
|
አዲስ አበባ ይድነቃቸዉ መኮንን በፊስ ቡክ ያስቀመጡት አስተያየት ነዉ።
|
ሰሞኑን በተለይ መገናኛ ብዙኃን ሲቀባበለዉ የነበረዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ንግግር ነበር።
|
ግልጽ ደብዳቤለክቡር ጠ ሚንስትር ዶር ዐብይ አህመድ በአሜሪካ ከምንገኝ ተቆርቋሪ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሲሉ ኢትዮጵያዉያን መልክት አስተላለፉ።
|
ይድረስ ለ ቱ ዳያስፖራ ኣቤቱታ እቅራቢዎች ግልፅ ደብዳቤ በሚል ርዕስ።
|
ይላል ነፃነት ኪዳኔ የተባሉ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ተጠቃሚ ባስቀመጡት አስተያየት ደግሞ እስክንድር ትናንት አባቶችህንም በብእሩ ነው ያስቀዘናቸው።
|
አሁንም በሀሳብ ልዕልና እንጂ ወጣቶችን ወደ አላስፈላጊ ረብሻ የሚነዳ መደዴ አይደለም።
|
ይፋታኤል አቤል የተባሉ ተጠቃሚ በበኩላቸዉ በአደባባይ ገጀራ ይዞ የወጣን ቄሮ ዝም ብሉ።
|
በስላማዊ መንገድ የሚታገለውን የአዲስ አበባ ህዝብን እና እስክንድርን ለማስፍራራት መሞከር ከአብይ አይጠበቅም።
|
ዶ ር አብይ ባላደራ የተባለው ባልደራስ ከመሰብሰብ ውጭ ምን ችግር ፈጥሮ ነው እንደዚህ አይነት ጨዋታ አንፈልግም የተባለዉ
|
የለገጣሮ ቤት ሲፈርስ ያልሰማ ሰው አንድ አዳራሽ ውስጥ የነበረን ተሰብሳቢ እንዴት ተማህ
|
ድንጋይ፡ ሜንጫና ሚስማር በሀገሪቱ መዲናና ከተሞች ይዞ የሚወጣውን ለማስንጠንቀቅ ለምን ዳር ዳር ተባለ፡፡
|
አይጥ በበላ ዳዋ ተመታ ነው ወይስ አይጥ ለሞቷ የድመት አፋንጫ ታሸታለች ነው፡፡
|
ጃሳ ኖሚና የተባሉ ተከታታይ በበኩላቸዉ አብይ በየዕለቱ የሚወገዘው ፡ የሚሰደበው በእርግጥም እስከዛሬ ከነበሩት የተሻለ መሪ ሰለሆነ ነው፡፡
|
የመናገር የመፃፍ የመደራጀት ነፃነት በር ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ስለከፈተ ነው፡፡
|
ዛሬ ያገኘነው ነፃነት እስከ ዛሬ ያላየነውና ያልለመድነው ሆኖ ነው አብይን ደካማ መሪ ያሰመሠለብን፡፡
|
አቶ ታከለ ይሄን የማሸጋገር ሂደት በሚመለከት በትክክል ያልሰራው ነገር አለ ከተባለ ሂስ ማቅረብ ጥሩ ነው።
|
ዋና ተግባራችን ለሚቀጥለው ምርጫ በአዲስ አበባ ዙሪያ ጥሩ አቋም እና የነዋሪዎቿን መብት ያስጠብቃል ያልነውን ፓርቲ ህዝቡ እንዲመርጠው ግፊት ማድረግ ነው።
|
ግድግዳ ጡፍ ወይም ግራፊቲ በሐዋሳ ከተማ በምዕራቡ ሀገራት የግድግዳ ጡፍ ወይም ግራፊቲ እንደ ተመልካቹ እና ማህበረሰቡ አተረጓጎም ይለያያል።
|
አንዳንዶች ግራፊቲን ከውንብድና ጋር ሲያገናኙ ሌሎች ስሜት የሚገለፅበት አንድ መንገድ እንደሆነ ይናገራሉ።
|
ሐዋሳ ከተማ የሚገኙ የተወሰኑ ወጣቶች የግድግዳ ጡፍን እንደ አንድ የስዕል ጥበብ ነድፈው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ።
|
የጣሊያንኛው ቃል ግራፊቶ ለብዙዎች ግራፊቲ በድንጋይ ላይ ተጫጭሮ የሚቀረፅ ጹሁፍ ወይም ምስል እንደማለት ነው።
|
በሐዋሳ ከተማ ግራፊቲ ኢትዮጵያ የወጣቶች ማህበር ብለው አንድ ማህበር በመመስረት ላይ ያሉ ወጣቶች እንደዚህ አይነቱ አሳሳል ዛሬ በከተማዋ የሚታወቁበት ሆኗል።
|
በሐዋሳ ከተማ የ ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው በሁሉም ለስዕል የተለየ ፍቅር እንዳለው ይናገራል።
|
ምንም እንኳን በሁሉም እና ባልደረቦቹ የግራፊቲ ስልቱን ከምዕራቡ ሀገራት ቢወስዱም ስራቸውን ለመስራት ባለቤቱን ፍቃድ ጠይቀው ነው።
|
አብዛኞቹም የግድግዳ ጸሀፊዎች እንይያዙ ስለሚፈሩ የሚፅፉት ወይም የሚስሉት ሌሊት ነው ።
|
በሐዋሳ ከተማ የግድግዳን ጡፍ ወይም ግራፊቲን እንደ አንድ የአሳሳል ስልት ከሚያየው ሌላው ወጣት አንዱ የበሁሉም ጓደኛ በረከት ተሾመ ነው።
|
በረከት በቴክኒክ ሙያ ተመርቆ ኮምፒውተር እና ተንቀሳቃሽ ስልኮችን ይጠግናል።
|
እሱም የግድግዳ ጡፍን የሚገልፀው እንደ በሁሉም ሀሳብን ለመግለፅ ነው።
|
በሁሉም እንደገለጸልን የ ግራፊቲ ኢትዮጵያ የወጣቶች ማህበር አባላት ራሳቸውን ለሌሎች የሚያስተዋውቁበት የመረጃ ገፅ በአሁኑ ሰዓት በማዘጋጀት ላይ ይገኛሉ።
|
ወጣቶቹ ሙያቸውን ለማዳበር ፌስ ቡክ እና ዩ ቱይፕ ከመሳሰሉ የማህበራዊ መገናኛ ድረ ገፆች መረጃ ያፈላልጋሉ።
|
ከዚህም በተጨማሪ አንዳንድ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ሀገር ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ወደእነሱም ብቅ ይሉ እና ሀሳብ ይለዋወጣሉ።
|
የትግራይ ተቃዋሚ አባላት አሁንም እንደታሰሩ ነዉ ይዘት ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
የቀድሞዉ የወታደራዊ ደሕንነት ከፍተኛ መኮንን የስቃይ ታሪክ አውዲዮውን ያዳምጡ።
|
ካሪቡኒ የሙዚቃ ቅንብሩ በአፍሪቃ የሚነገሩ ተረቶችን ምሳልያዊ አነጋገሮችን የአፍሪቃን ሁኔታ በታሪክ መልክ እያስረዳ ነዉ አስከትሎ ዜማዉን የሚያስደምጠዉ።
|
ለወባ ክትባት ምርምር በጎርጎሪዮሳዊዉ ዓ ም በዓለም ዙሪያ በወባ በሽታ ሺ ሰዎች ማለቃቸዉን የዓለም የጤና ድርጅት ያመለክታል።
|
ኑሮ እጅግ ከመጠን በላይ ከብዷል እናም አስቸኳይ መፍትሄ እና አንድ እልባት ሊበጅለት ይገባል ይላሉ ያነጋገርናቸው አስተያየት ሰጭዎች።
|
አዲስ ወረርሽን በድሬደዋ ምሥራቅ ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተው በሽታ ብዙዎችን ማዳረሱ እየተነገረ ነው።
|
የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የጤና ቢሮ ኃላፊ እስካሁን በአዲሱ በሽታ ከ ሺህ ሰዎች በላይ በመያዛቸው በከተማው ወረርሽኝ መከሰቱን ይፋ አድርገዋል።
|
የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሠራተኞች እሮሮ የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሠራተኞች በአሠሪዎቻቸው የተለያዩ የመብት ጥሰቶች እንደሚፈጸሙባቸው ገለጹ፡፡
|
ድንጋይ ይወረዉሩ እንደነበር የተገለጸዉን የቡድኑን ደጋፊዎች ለመበተንም ፖሊስ የሚያስለቅስ ጭስ ተጠቅሟል።
|
የግብፁ ሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር አንጋፋና እድሜ ጠገብ ስብስብ መሆኑ ነዉ የሚገለጸዉ።
|
የሽግግር መንግስቱ ሙስሊም ወንድማማቾችን በአሸባሪነት የፈረጀዉ በአንድ የፖሊስ ሕንፃ ላይ አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰዉ ጥቃት የ ሰዎች ህይወት ካለፈ በኋላ ነዉ።
|
ሌላ አንድ ጀሃዳዊ ቡድን ለድርጊቱ ኃላፊነቱን ቢወስድም በይፋ ተጠያቂ የሆነዉ የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር ነዉ።
|
የግብፅ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆሳም ኤይሳ እንዲህ ነዉ ያሉት መንግስት እንደገና ወደኋላ መመለስ የማይችል መሆኑን በድጋሚ ማረጋገጥ ይሻል።
|
ስለሆነም መንግሥት በሕገ መንግሥት አንቀጽ የወንጀለኛ መቅጫ ደንብ መሠረት የሙስሊም ወንድማማችነት ማህበር አባላት አሸባሪዎች ድርጅቱም አሸባሪ ነው።
|
ስለሆነም እርሱን በጽሑፍም ሆነ በቃል የሚያበራታቱ ወይም በሌላ ዓይነት መንገድ የሚረዱና ተግባሩን በገንዘብ የሚደግፉ የወንጀል ተባባሪዎች ናቸው።
|
እንዲሁም በአንቀጽ የተገለጠው ቅጣት በማንም ተባባሪ ግለሰብም ሆነ ቡድን ላይ ተፋጻሚ ይሆናል ።
|
ሙስሊም ወንድማማቾች በአሸባሪነት መፈረጁን በማዉገዝ ሰላማዊ ተቃዉሞዉን እንደሚቀጥልበት አስታዉቋል።
|
መንግሥት ሙስሊም ወንድማማቾችን የወነጀለበትን ፍንዳታ ያደረሰዉ ሌላ ቡድን ነዉ።
|
ዋና ከተማ ካይሮ አንድ ጓዳ ሠራሽ ፈንጂ በህዝብ መጓጓዣ አቅራቢያ ፈንድቶ አምስት ሰዎች ከቆሰሉ በኋላ ዉጥረት ነግሶባታል።
|
መንግስት ረቡዕ ዕለት ቡድኑን በአሸባሪነት ከመዘገበ በኋላ እሱን በመደገፍ አደባባይ የሚወጣ ሰልፈኛን እንደማይታገስ ፖሊስ ዝቷል።
|
ዛሬ ከካይሮ የወጡ ዘገባዎች አልአዝሃር ዩኒቨርሲቲ ጊቢ የተማሪዎች ማደሪያ ዉስጥ ጭስ ይታይ እንደነበር ያመለክታሉ።
|
የአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ፖሊሶች አስለቃሹን ጭስ ከተኮሱ በኋላ ሁኔታዉ መከተሰቱን ነዉ የገለፀዉ።
|
የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር አባል የነበሩት የቀድሞዉ ፕሬዝደንት ሞሐመድ ሙርሲ እስር ላይ ናቸዉ።
|
ከእሳቸዉ ሌላም የቡድኑ አመራር አካላት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ወህኒ ወርደዋል።
|
ሙርሲ ከስልጣን ከተነሱበት ካለፈዉ ሐምሌ ወር አንስቶም ሙስሊም ወንድማማቾች ባለማቋረጥ የተቃዉሞ ሰልፉን ቀጥሎበታል።
|
የግብፅ የፀጥታ ኃይሎች በመላ ሀገሪቱ ዛሬ ለሰልፍ ከወጡ ደጋፊዎች ጋ ተጋጭተዋል ከመቶ በላይ ሰዎችን አስረዋል።
|
ካይሮ ዉስጥ መሳሪያ የተጠመደባቸዉ ተሽከርካሪዎች የከተማዉን ዋና አደባባይ መንገድ ዘግተዋል።
|
ሙርሲ ከስልጣን ከወረዱ ወዲህ በየጊዜዉ ተመሳሳይ የተቃዉሞ ሰልፉ ቀጥሏል ሰልፉን ለመበተን በሚወሰድ ርምጃም በሺዎች የሚገመቱ ሰዎች ህይወት አልፏል።
|
በተለይ በከፍተኛ ስልጣን ላይ የነበሩት አባላቱ በየሰላማዊ ሰልፉ ለሞቱ በተጠያቂነት በሀገር ክህደት እንዲሁም በአሸባሪነት ክስ ተመስርቶባቸዋል።
|
በአዲስ አበባ ዙሪያ ጥሩ አቋም እና የነዋሪዎቿን መብት ያስጠብቃል ይዘት ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ጤና እና አካባቢ አነጋጋሪዉ የሴቶች መብት ይዞታ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከትናንት በስተያ ታስቦ ዉሏል።
|
ዘንድሮ የሴቶች ቀን ሲታሰብም የተመረጠዉ መሪ ቃል እዉን አድርጉት የሚል ነዉ።
|
በዚህ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለሴቶች መብት ለሚደረገዉ ትግል የተደረሰዉን መሠረታዊ ስምምነት ኛ ዓመትም እናከብራለን።
|
ይህም ለፆታ እኩልነትና በተለያዩ ሙያዎችና ማኅበራዊ ዘርፎች ሴቶችና ልጃገረዶች ለአመራር ብቁ እንዲሆኑ ግልፅ አቅጣጫን አመላካች ነዉ።
|
በርካታ ልጃገረዶች በፊት ከነበረዉ በተሻለ መልኩ ትምህርት የማግኘት እድል አግኝተዋል በወሊድ ጊዜ የሚሞቱ እናቶች ቁጥር ከዚህ ቀደም ከነበረዉ በግማሽ ቀንሷል።
|
በርካታ ሴቶች በንግዱ ዓለም በመንግሥት አስተዳደርና በዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ዉስጥ የመሪነት ቦታ ይዘዋል።
|
አሁም ግን ሴቶች ሊደርሱባቸዉ የሚገባ በርካታ ግቦች አሉ እንደየቤት ዉስጥ ጥቃት ግርዛት እንዲሁም የተለያዩ የጥቃት ዓይነቶች።
|
አድሎ አሁንም ጣሪያ እንደነካ ነዉ ይህን ሁሉ ተባብረን ማስቀረት ይኖርብናል።
|
በማለት ነዉ ዕለቱን አስመልክተዉ የተመድ ዋና ፀሐፊ ባን ጊ ሙን መልዕክታቸዉን ያስተላለፉት።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.