doc_no
int64
1
12.6k
doc_text
stringlengths
81
395k
relevant_topic_nos
sequencelengths
0
1
relevant_topic_titles
sequencelengths
0
1
relevant_topic_descriptions
sequencelengths
0
1
relevant_topic_narratives
sequencelengths
0
1
401
አዲሱ የአምቦ አውቶብስ መናኸሪያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ስራ ይጀምራል…የከተማው ትራንስፖርት ባለስልጣን 201 Share አምቦ ግንቦት 21/2011 በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ከተማ በ56 ሚሊዮን ብር በጀት ግንባታው በመካሔድ ላይ ያለው የአምቦ ዘመናዊ የአውቶብስ መናኸሪያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ስራ ይጀምራል ተባለ። የአምቦ ከተማ ትራንስፖርት ባለስልጣን ኃላፊ አቶ ቦጃ ወልደ ሚካኤል እንደገለጹት በ12 ሺህ ካሬ ሜትር በላይ በያዘው ቦታ ላይ እየተገነባ ያለው መናኸሪያ የቢሮ ሕንጻ የተገልጋይ ማረፊያ፣ካፌ፣የመረጃ ማዕከልና ለመንግደኞች መስተንግዶ የሚያስፈልጉ አገልግሎቶች የተሟሉለት ነው። ከሶስት አመታት በፊት የግንባታ ስራው የተጀመረው የአምቦ አውቶብስ መናኸሪያ ባለፈው ዓመት ለአገልግሎት ይበቃል ተብሎ ቢታቀድም በተቋራጩ አቅም ማነስ ምክንያት ስራው መጓተቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ የግንባታው ስራ ከ95 ከመቶ በላይ መጠናቀቁን ገልጸው “አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል” ብለዋል ፡፡ መናኸሪያው ቀደም ሲል በከተማው ይታይ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር እንደሚያቃልል ገልጸዋል። የአዲሱ መናኸሪያ መገንባት የትራንስፖርት አገልግሎትን ከማሳለጥ ባለፈ የንግዱን እንቅስቃሴ በማጠናከር ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደሚያስገኝ የገለጹት ደግሞ የአምቦ ከተማ አስተዳደር ካንቲባ አቶ ተረፈ በዳዳ ናቸው። “ግንባታው በአሁኑ ወቅት ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለ700 ወጣቶች ተጨማሪ የስራ እድል ይፈጥራል”ብለዋል። በአካባቢው የሚኖር ወጣት ኒሞና ፈይሳ በበኩሉ የመናኸሪያው መሰራት ለሱና ለሌሎች ወጣቶች የስራ እድል እንደሚፈጥር እምነቱን ገልጿል፡፡ በአምቦ ቀበሌ 02 አካባቢ የተገነባው የአውቶቢስ መናሃሪያ በአንድ ጊዜ እስከ 600 አሽከርካሪዎችን ማስተናገድ እንደሚችል ከባለስልጣኑ የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
402
ተቋርጦ የቆየው የሻምቡ መናኸርያ ግንባታ ሊጀመር ነው በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ከሰባት አመት በፊት ግንባታው ተጀምሮ የተቋረጠውን የሻምቡ ከተማ መናኸሪያ መልሶ ለማስጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን የዞኑ የትራንስፖርት ባለሥልጣን አስታወቀ ፡፡ የባለሥልጣኑ ምክትል ኃላፊ አቶ ጅራ አብዲሣ እንዳስታወቁት የመናኽርያ ግንባታ ስራው በመቋረጡ በነዋሪው ዘንድ የፈጠረውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ግንባታውን ማስቀጠል አስፈልጓል ። የክልሉ ትራንስፖርት ባለሥልጣን በመደበው 35 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጭ በ2003 አም የተጀመረው የመናኽርያ ግንባታ ስራ 55 በመቶ መጠናቀቁንና 48 በመቶ ክፍያ የተፈፀመበት መሆኑን አስታውሰዋል ። ተቋራጩ በነበረበት የአቅም ማነስ ውሉ እንዲቋረጥ ቢደረግም በወቅቱ ለሌላ ተቋራጭ ሳይሰጥ ለረዥም አመት በመቆየቱ በነዋሪው ዘንድ ቅሬታ ማሳደሩን ተናግረዋል ። የነዋሪውን ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በወጣ ጨረታ መሰረት አይኬን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ግንባታውን በ28 ሚሊዮን ብር ለማጠናቀቅ ጨረታውን አሸንፏል፡፡ "የመናኸሪያው ግንባታ በስምንት ወር ውሰጥ ይጠናቀቃል" ያሉት ኃላፊው መናኸሪያው ከተሽከርካሪ ማቆሚያ በተጨማሪ ለመንገደኞች ማረፊያ፣ ለሱቅ፣ ካፍቴሪያና ጽህፈት ቤትን ጨምሮ ለተለያየ አገልግሎት የሚሆኑ ክፍሎች እንደሚኖሩት አመላክተዋል።
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
403
ተቋርጦ የቆየው የሻምቡ መናኸርያ ግንባታ ሊጀመር ነው በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ከሰባት አመት በፊት ግንባታው ተጀምሮ የተቋረጠውን የሻምቡ ከተማ መናኸሪያ መልሶ ለማስጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን የዞኑ የትራንስፖርት ባለሥልጣን አስታወቀ ፡፡ የባለሥልጣኑ ምክትል ኃላፊ አቶ ጅራ አብዲሣ እንዳስታወቁት የመናኽርያ ግንባታ ስራው በመቋረጡ በነዋሪው ዘንድ የፈጠረውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ግንባታውን ማስቀጠል አስፈልጓል ። የክልሉ ትራንስፖርት ባለሥልጣን በመደበው 35 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጭ በ2003 አም የተጀመረው የመናኽርያ ግንባታ ስራ 55 በመቶ መጠናቀቁንና 48 በመቶ ክፍያ የተፈፀመበት መሆኑን አስታውሰዋል ። ተቋራጩ በነበረበት የአቅም ማነስ ውሉ እንዲቋረጥ ቢደረግም በወቅቱ ለሌላ ተቋራጭ ሳይሰጥ ለረዥም አመት በመቆየቱ በነዋሪው ዘንድ ቅሬታ ማሳደሩን ተናግረዋል ። የነዋሪውን ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በወጣ ጨረታ መሰረት አይኬን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ግንባታውን በ28 ሚሊዮን ብር ለማጠናቀቅ ጨረታውን አሸንፏል፡፡ "የመናኸሪያው ግንባታ በስምንት ወር ውሰጥ ይጠናቀቃል" ያሉት ኃላፊው መናኸሪያው ከተሽከርካሪ ማቆሚያ በተጨማሪ ለመንገደኞች ማረፊያ፣ ለሱቅ፣ ካፍቴሪያና ጽህፈት ቤትን ጨምሮ ለተለያየ አገልግሎት የሚሆኑ ክፍሎች እንደሚኖሩት አመላክተዋል።
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
404
በባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የሚገኘው የአውቶቡስ መናኸሪያና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በመበላሸታቸው ተገቢውን አገልግሎት እንደማይሰጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች አስታወቁ፡፡ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የተሽከርካሪዎች ባለንብረቶችና ሾፌሮች ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በከተማዋ የሚያልፈውን 10 ኪሎ ሜትር ዋና የመኪና መንገድን ጨምሮ ለውስጥ ለውስጥ መንገዶች ተገቢው ጥገና ባለመደረጉ በከፍተኛ ሁኔታ በመበላሸታቸው ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ወደማይችሉበት ደረጃ ደርሰዋል፡፡ በመሆኑም በከተማዋ ይሰሩ የነበሩ ታክሲዎች አገልግሎታቸውን ወደ ጎባ መስመር በመቀየራቸው በከተማዋ የታክሲ አገልግሎት በመቋረጡ ለችግር መዳረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም በከተማዋ የሚገኘው የአውቶቢስ መናኻሪያ ያለ እድሳት ለረጅም ጊዜ በማገልገሉ ምክንያት ተበላሽቶ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት ባለመቻሉ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶች በየመንገዱ ላይ ቆመው ሰው ለማሳፈር መገደዳቸውን ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ገልጸዋል፡፡ የሮቤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የአስተዳደርና ፋይናንስ ኃላፊ አቶ አህመድ ሁሴን ስለጉዳዩ ተጠይቀው ባጋጠመው የበጀት እጥረት የአውቶቡስ መናኸሪያውም ሆነ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ባለመጠገናቸው ችግሩ መከሰቱን ገልጸው በዚህ ዓመት ግን ተገቢውን የጥገና ስራ ለማከናውን በቂ በጀት የተመደበ ስለሆነ ችግሩ ይወገዳል ብለዋል፡፡
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
405
የቃሊቲ መናኸሪያ እና የቃሊቲ ትራንስፖርት ማኔጅመንትና የትራፊክ ደህንነት ማሰልጠኛ ተቋም ግንባታ ተጀመረ On Apr 4, 2019 621 አዲስ አበባ፣ የካቲት 26 ፣2011 (ኤፍ.ቢ.ሲ )የቃሊቲ መናኸሪያ እና የቃሊቲ ትራንስፖርት ማኔጅመንትና የትራፊክ ደህንነት ማሰልጠኛ ተቋም ግንባታ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል። በስነ ስርዓቱ ላይም የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሙሉ ገብረእግዚአብሄር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ። በዚህ ወቅትም የትራንሰፖርት ዘረፉን በእውቀት እና በክህሎት እንዲመራ ለማድረግ የተቋሞቹ መገንባት ፋይዳው ከፍ ያለ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሙሉ ገብረእግዚአብሄር ተናግረዋል። ከዚህ ባለፈም የሚገነቡት ፕሮጀክቶች ቃሊቲ መናኸሪያ ዙሪያ ያሉትን ችግሮች በመፍታት ረገድ የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ነው የገለጹት። እንዲሁም የቃሊቲ መናኸሪያ ያሉበት ችግሮችን ለመቅረፍ የመናኸሪያ አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና የተገልጋይዮችን ምቾት የጠበቀ ለማድረግ ያስችላል ነው የተባለው። ለቃሊቲ መናኸሪያ ግንባታ 445 ሚሊየን ብር በጀት የተያዘለት መሆኑን የገለጹት ወይዘሮ ሙሉ ፥ግንባታውን አጠናቆ ለመጨረስም የአንድ ዓመት ከ6 ወር ጊዜ መቀመጡን አንስተዋል። በተጨማሪም ለቃሊቲ ትራንሰፖርት ማኔጅመንትና የትራፊክ ደህንነት ማሰልጠኛ ተቋም ግንባታ 382 ሚሊየን ብር በጀት የተመደበ ሲሆን፥ ግንባታውም በ2013 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። የኢንስቲትዩቱ መገንባት የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የሚያስችሉ ጥናትና ምርምሮች የሚደረጉበትና በመንገድ ትራንስፖረት ዘርፍ መንግስታዊም ሆኑ መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት ስልጠና ለመስጠት ያስችላል ተብሏል፡፡ በዚህም ለህዝብና ጭነት ትራንስፖርት ማህበራት፣ ድርጅቶች፣ ለሁሉም የትራንስፖርት ተቋማት በትራንስፖርት ኦፕሬሽን፣ በትራፊክ ሴፍቲ፣ በትራንሰፖርት ማኔጅመንት፣ በትራንስፖርት ኢንጂነሪንግ እና ሌሎችም የትራንስፖርት መስኮች ስልጠናዎችን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑ ነው የተገለፀው።
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
406
የኮምቦልቻ ከተማ መናኸሪያ በኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ ለተያዙ ሴቶች ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚ እያደረገ ነው ----------------------------------------------------------------------------------------- የኮምቦልቻ መናኸሪያ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ምቹና የተቀላጠፈ ከማድረግ ባሻገር በኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ የተያዙ 16 ሴቶችን በመናኸሪያ ውስጥ የመስሪያ ቦታ በመስጠትና ድጋፍ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያደረገ ነው:; በከተማው መናኸሪያ አስተዳደር አማካይነት በ2000 ዓ.ም ሰላም የምግብ ዝግጅትና የግል ማህበር በሚል የተደራጁት እነዚህ ሴቶች በጥቂት ካፒታል ስራውን የጀመሩ ሲሆን አሁን ቋሚ ንብረታቸውን ሳይጨምር 127,000 ብር ካፒታል ደርሰዋል:: የማህበሩ ሰብሳቢ የሆነችው ወ/ሮ አበበች አሊ እንደገለፀችው ማህበሩ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለመናኸሪያው ማህበረሰብ የምግብና የሻይ ቡና አገልግሎት በመስጠት የማህበሩ አባላት እራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት ችለዋል ብላለች:: በተጨማሪም ማህበሩ ከሚያገኝው ትርፍ በየወሩ 10 ለሚሆኑ ቫይረሱ ለአለባቸው ህጻናት 150 ብር ድጋፍ እያደረገላቸው እንደሚገኝ ተገልጿል:: የማህበሩ አባላት ለመናኸሪያው ማህበረሰብ የሻይ ቡና ፕሮግራም በማዘጋጀትና በተለያዪ በዓላት ትውልድ ይዳን በኛ ይብቃ በሚል እራሳቸውን ይፋ አድርገው በቫይረሱ ዙረያ ትምህርትና ግንዛቤ የመስጠት ስራ ይሰራሉ:: የከተማው አስተዳደር ጥቃቅንና አነስተኛ ልማት ኢንተርፕራይዝ በበኩሉ በሂሳብ አያያዝ ስልጠና በመስጠት እንዲሁም የከተማው አስተዳደር የተለያዩ ጨረታዎችን ላይ እንዲሳተፉ ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን የማህበሩ ስብሳቢ ገልጻለች::
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
407
የአዳማ መናኸሪያ በዘጠኝ ሚሊዮን ብር የማስፋፊያ ግንባታ ሊደረግለት ነው 8 October 2017 ታደሰ ገብረማርያም ግንባታው ከሁለት ወር በኋላ ይጀመራል ከተቋቋመ ከ30 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የአዳማ መናኸሪያ በዘጠኝ ሚሊዮን ብር የማስፋፊያ ግንባታ ሊደረግለት ነው፡፡ አዲስ መናኸሪያም ተዘጋጅቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው፡፡ የአዳማ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቃሲም ኡስማን እንደገለጹት፣ መናኸሪያውን ለማስፋፋት ያስፈለገበት ምክንያት በየጊዜው ቁጥራቸው እየጨመሩ የመጡትን ተሽከርካሪዎችና ተጓዦች ማስተናገድ ከአቅሙ በላይ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የቀድሞው መናኸሪያ ስፋት 18 ሺሕ 700 ካሬ ሜትር ሲሆን፣ በቀን ሁለት ሺሕ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ ላይ ይገኛል፡፡ የማስፋፊያው ግንባታ ሲጠናቀቅ የቅጥር ግቢው ስፋት ወደ 22 ሺሕ ካሬ ሜትር ያድጋል፡፡ ተሽከርካሪ የማስተናገድ አቅሙም በቀን ከአራት ሺሕ በላይ ይሆናል፡፡ አዲሱ መናኸሪያ የተዘጋጀው ወደ አሰላ በሚያቀናው መንገድ በሚገኘውና 02 ቀበሌ ወይም ኒግራ (ረቡዕ ገበያ) እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ሲሆን፣ የመናኸሪያውም ስፋት 11 ሺሕ ካሬ ሜትር መሆኑን አቶ ቃሲም ገልጸዋል፡፡ በኅብረተሰቡ ተሳትፎ የተዘጋጀው ይህ መናኸሪያ በቀን አንድ ሺሕ ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ አቅም እንዳለውና መፀዳጃ ቤቶች፣ የቲኬት መሸጫና የማኅበራት ቢሮዎች ያሉት መሆኑን አቶ ቃሲም አመልክተው፣ እነዚህን መገልገያዎች ለማሠራት፣ የግቢውን ዙሪያ በግንብ አጥር ለመከለልና የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማስገባት በጠቅላላው 222 ሺሕ ብር ወጪ መደረጉን አስረድተዋል፡፡ የማስፋፊያ ግንባታ የሚካሄድበት መናኸሪያ ሞጆ፣ ቢሾፍቱ፣ አዲስ አበባ፣ ዝዋይ ሻሸመኔ እንዲሁም 02 ቀበሌ ውስጥ የተዘጋጀው ሌላው መናኸሪያ ሐረሪ፣ ሐዋሳ፣ ድሬዳዋ፣ አሰላ፣ ኢተያ ወዘተ ለሚመላለሱ ተሽከርካሪዎች መነሻና መድረሻ ሆነው በማገልገል ላይ መሆናቸውን አቶ ቃሲም ተናግረዋል፡፡
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
408
አዲሱ የአምቦ አውቶብስ መናኸሪያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ስራ ይጀምራል…የከተማው ትራንስፖርት ባለስልጣን አምቦ ግንቦት 21/2011 በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ከተማ በ56 ሚሊዮን ብር በጀት ግንባታው በመካሔድ ላይ ያለው የአምቦ ዘመናዊ የአውቶብስ መናኸሪያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ስራ ይጀምራል ተባለ። የአምቦ ከተማ ትራንስፖርት ባለስልጣን ኃላፊ አቶ ቦጃ ወልደ ሚካኤል እንደገለጹት በ12 ሺህ ካሬ ሜትር በላይ በያዘው ቦታ ላይ እየተገነባ ያለው መናኸሪያ የቢሮ ሕንጻ የተገልጋይ ማረፊያ፣ካፌ፣የመረጃ ማዕከልና ለመንግደኞች መስተንግዶ የሚያስፈልጉ አገልግሎቶች የተሟሉለት ነው። ከሶስት አመታት በፊት የግንባታ ስራው የተጀመረው የአምቦ አውቶብስ መናኸሪያ ባለፈው ዓመት ለአገልግሎት ይበቃል ተብሎ ቢታቀድም በተቋራጩ አቅም ማነስ ምክንያት ስራው መጓተቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ የግንባታው ስራ ከ95 ከመቶ በላይ መጠናቀቁን ገልጸው “አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል” ብለዋል ፡፡ መናኸሪያው ቀደም ሲል በከተማው ይታይ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር እንደሚያቃልል ገልጸዋል። የአዲሱ መናኸሪያ መገንባት የትራንስፖርት አገልግሎትን ከማሳለጥ ባለፈ የንግዱን እንቅስቃሴ በማጠናከር ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደሚያስገኝ የገለጹት ደግሞ የአምቦ ከተማ አስተዳደር ካንቲባ አቶ ተረፈ በዳዳ ናቸው። “ግንባታው በአሁኑ ወቅት ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለ700 ወጣቶች ተጨማሪ የስራ እድል ይፈጥራል”ብለዋል። በአካባቢው የሚኖር ወጣት ኒሞና ፈይሳ በበኩሉ የመናኸሪያው መሰራት ለሱና ለሌሎች ወጣቶች የስራ እድል እንደሚፈጥር እምነቱን ገልጿል፡፡ በአምቦ ቀበሌ 02 አካባቢ የተገነባው የአውቶቢስ መናሃሪያ በአንድ ጊዜ እስከ 600 አሽከርካሪዎችን ማስተናገድ እንደሚችል ከባለስልጣኑ የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
409
አዲሱ የአምቦ አውቶብስ መናኸሪያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ስራ ይጀምራል…የከተማው ትራንስፖርት ባለስልጣን አምቦ ግንቦት 21/2011 በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ከተማ በ56 ሚሊዮን ብር በጀት ግንባታው በመካሔድ ላይ ያለው የአምቦ ዘመናዊ የአውቶብስ መናኸሪያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ስራ ይጀምራል ተባለ። የአምቦ ከተማ ትራንስፖርት ባለስልጣን ኃላፊ አቶ ቦጃ ወልደ ሚካኤል እንደገለጹት በ12 ሺህ ካሬ ሜትር በላይ በያዘው ቦታ ላይ እየተገነባ ያለው መናኸሪያ የቢሮ ሕንጻ የተገልጋይ ማረፊያ፣ካፌ፣የመረጃ ማዕከልና ለመንግደኞች መስተንግዶ የሚያስፈልጉ አገልግሎቶች የተሟሉለት ነው። ከሶስት አመታት በፊት የግንባታ ስራው የተጀመረው የአምቦ አውቶብስ መናኸሪያ ባለፈው ዓመት ለአገልግሎት ይበቃል ተብሎ ቢታቀድም በተቋራጩ አቅም ማነስ ምክንያት ስራው መጓተቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ የግንባታው ስራ ከ95 ከመቶ በላይ መጠናቀቁን ገልጸው “አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል” ብለዋል ፡፡ መናኸሪያው ቀደም ሲል በከተማው ይታይ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር እንደሚያቃልል ገልጸዋል። የአዲሱ መናኸሪያ መገንባት የትራንስፖርት አገልግሎትን ከማሳለጥ ባለፈ የንግዱን እንቅስቃሴ በማጠናከር ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደሚያስገኝ የገለጹት ደግሞ የአምቦ ከተማ አስተዳደር ካንቲባ አቶ ተረፈ በዳዳ ናቸው። “ግንባታው በአሁኑ ወቅት ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለ700 ወጣቶች ተጨማሪ የስራ እድል ይፈጥራል”ብለዋል። በአካባቢው የሚኖር ወጣት ኒሞና ፈይሳ በበኩሉ የመናኸሪያው መሰራት ለሱና ለሌሎች ወጣቶች የስራ እድል እንደሚፈጥር እምነቱን ገልጿል፡፡ በአምቦ ቀበሌ 02 አካባቢ የተገነባው የአውቶቢስ መናሃሪያ በአንድ ጊዜ እስከ 600 አሽከርካሪዎችን ማስተናገድ እንደሚችል ከባለስልጣኑ የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
[ 105 ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ" ]
[ "የመናኸርያ ግንባታ ስለተደረገባቸው አካባቢወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት ፡፡" ]
[ "ስለ አዳዲስ መናኸርያ ግንባታወችና ስለተመደበላቸው በጀት, ስለ ተበላሹ መናኅሪያወች ጥገና የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ መንገድና ስለቤት ግንባታ, ስለ አወቶቢስ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
410
በሶማሌ ለመጠጥ ውሃ እጥረት ለተጋለጡ ወገኖች ውሃ በቦቴ እየተሰራጨ ነው ሩብ ሚሊየን ወገኖች የውሃ እጥረት ገጥሟቸዋል ። በሶማሌ ክልል ለመጠጥ ውሃ እጥረት ለተጋለጡ ሩብ ሚሊየን ያህል ነዋሪዎች ውሃ በቦቴ ማሰራጨት መጀመሩን የክልሉ አደጋ መከላከል ፣ ሰራተኛና ማሀበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ ። የቢሮው ሃላፊ አቶ መሀመድ ረሺድ ትናንት ለዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል እንደገለጹት ቢሮው በመደበው 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር 12 ቦቴዎችን ተከራይቶ በዘጠኙም ዞኖች ለሚገኙ ተረጂዎች ሰሞኑን ውሃ በማሰራጨት ላይ ነው ። የፌዴራል አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚሽን አምስት ተጨማሪ ቦቴዎች ወደ ክልሉ በመላክ የውሃ ስርጭቱን በማጠናከር ላይ እንደሆነ ገልጸው ፤ ዩኒሴፍም ለሀርቲሼክ ፣ ቀብሪ በያህና ፋፈን መጠለያ ካምፖች ለሰፈሩ 20ሺ ተረጂዎች የመጠጥ ውሃ በማቅረብ ላይ መሆኑን ተናግረዋል ። ከችግሩ ስፋት አንጻር የክልሉ መንግስት 20 ተጨማሪ አዳዲስ ቦቴዎች ከውጭ በግዥ ማስመጣት ላይ ቢሆንም ፤ በአሁኑ ወቅት ቢሮውና ሌሎች እርዳታውን በማሰራጨት ላይ ባሉ ድርጅቶች እየተደረገ ያለው ትረት ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ ሃላፊው ትሪ አቅርበዋል ። ከውሃ አቅርቦቱ ጎን ለጎንም ለምግብ እህል እጥረት ለተጋለጡ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ተረጂዎች ከድሬዳዋና ናዝሬት የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚሽን መጋዘኖች እህልና የአልሚ ምግብ እርዳታ በመጓጓዝ ላይ መሆኑን አስረድተዋል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
411
በጂንካ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው, .._2012__. 0 302 226 ; 5; ጂንካ፤ መጋቢት 11 2004 ዋኢማ - በደቡብ ኦሞ ዞን ጂንካ ከተማ በ22 ሚሊዮን ብር ወጪ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ የዞኑ የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳች መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው ሃላፊ አቶ ከሪም ጀማል ለዋልታ እንደገለጹት  የፕሮጅክቱ ግንባታ መካሄድ የከተማዋን ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት በአስተማማኝ ደረጃ ለመፍታት ያስችላል፡፡ ፕሮጀክቱ ከተጀመረ ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ የ21 ኪሎ ሜትር የቧንቧ መስመር ዝርጋታ የተካሄደ ሲሆን በተመረጡ ቦታዎች ላይ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋኖችና የማከፋፈያ ቦኖዎች ግንባታ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ሃላፊው ተናግረዋል ፡፡ እስከአሁን የፕሮጀክቱ ግንባታ አፈጻጻም ከ 70 በመቶ በላይ መከናወኑና አጠቃላይ ሥራውም በመጪው ዓመት መጨረሻ ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክተዋል፡፡ ለፕሮጀክቱ ግንባታ ከሚውለው የ 22 ሚሊዮን ብር ውስጥ ግማሽ ያህሉ ከክልሉ መንግሥት የተመደበ ሲሆን ቀሪው በዓለም ባንክ ድጋፍ የሚሸፈን መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የመጠጥ ወሃ ፕሮጀክቱ ለአገልግሎት ሲበቃ ከ 26 ሺህ በላይ የሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች ቀደም ሲል ያጋጥማቸው የነበረውን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ከመቅረፉም በላይ የውሃው እጥረት በከተማዋ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ላይ ሲያሳድር የነበረውን ተጽኖ እንደሚያቃልል ጠቁመዋል፡፡ ፕሮጀክቱ እስከ መጪው 2020 ዓም ድረስ የከተማዋን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት በአስተማማኝ ሁኔታ ይሸፍናል ማለታቸውን ኃላፊውን ጠቅሶ ዋልታ ዘግቧል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
412
በአርባ ምንጭ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው, .._2012. 0 ; 5; አርባ ምንጭ፤ ሚያዝያ 15 2004 ዋኢማ - የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት በ77 ሚሊዮን ብር ወጪ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ  ውሃ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የጽሕፈት ቤቱ ተወካይ አቶ ፍፁም ገብረ ዮሐንስ ለዋልታ እንደገለጹት የፕሮጅክቱ ግንባታ  የከተማዋን ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት በአስተማማኝ ደረጃ ለመፍታት ያስችላል፡፡ ፕሮጀክቱ ከተጀመረ ካለፈው ዓመት ጀምሮ እስከአሁን ድረስ የቧንቧ መስመር ዝርጋታ፤ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋኖችና የማከፋፈያ ቦኖዎች ግንባታ መካሄዳቸውን  ተወካዩ ተናግረዋል ፡፡ እስከአሁን የፕሮጀክቱ ግንባታ አፈጻጻም ከግማሽ በላይ መከናወኑንና አጠቃላይ ሥራውም በ2005 ዓም ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተወካዩ አመልክተዋል፡፡ ለፕሮጀክቱ ግንባታ የሚውለው 77 ሚሊዮን ብር በወርልድ ባንክ የዘላቂ የንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የሚሸፈን መሆኑን ተወካዩ አስረድተዋል፡፡ የአርባምጭ ከተማ የውሃ አቅርቦት በ1980 ዓም በተዘረጋበት ወቅት የከተማው ሕዝብ ቁጥር 46 ሺህ ብቻ እንደነበር ያስታወሱት ተወካዩ በአሁኑ ወቅት የሕዝቡ ቁጥር ከ 100 ሺህ በላይ በመድረሱ የአቅርቦትና የፍላጎት አለመጣጣም ችግር መኖሩን ተናግረዋል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
413
በአንዳንድ አካባቢዎች የሚገኙ ሀይቆች የውሃ መጠን መቀነስ እንደሚስተዋልባቸው ተጠቆመ, .._2012_. 0 187 140 ; 5; አዲስ አበባ፤ ግንቦት 112004 (ዋኢማ) -  ስምጥ ሸለቆን ጨምሮ  በአንዳንድ አካባቢዎች የሚገኙ  ሀይቆች የውሃ መጠን መቀነስ እንደሚስተዋልባቸው የፌደራል የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ገለጸ። በሀይቁ አከባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎችም እንዳረጋገጡት በተለይም  ወደ ሀይቆቹ የሚገባ ደለል  ለውሃ መጠናቸው  መቀነስ ምክንያት እየሆነ ነው። ባለሰልጣኑ በአንፃሩ የውሃ መጠናቸው  እየጨመረ የመጡ ሀይቆች እንዳሉም ጠቁሟል። የፍቅር ሀይቅ ሀዋሳ  በየዕለቱ  ውበቱ የሚያስደምመውን  የፀሃይ መግቢያ  ለመመልከት የሚሰባሰቡትን አድናቂዎቹን እየዋሸ  ነው። ሀይቁ ያለ ይምሰል እንጂ የውሃ መጠኑ እየቀነሰ  ጥልቀቱ እያጠረ መምጣቱን  የሚናገሩ  የሀዋሳ  ከተማ ነዋሪዎች አሉ። በሃይቁ ዳርቻ የበቀሉት ቄጠማዎች በእጅጉ እየበዙ ዳርቻው እየሰፋ  መምጣቱን የሀይቁ  የዉሃ መጠን  ለመቀነሱ ማረጋገጫ መሆኑን ነዋሪዎች ይናገራሉ። አሁን ባለዉ ይዞታ ከቀጠለም የመድረቅ አደጋ ተጋርጦበታልም ይላሉ። አደጋዉ በሃዋሳ ሃይቅ ላይ ብቻ ያንዥበበ አይደለም። ሌሎች የሃገራችን አንዳንድ ሀይቆችም ስጋት አለባቸው። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሀይቅ ከተማ አካባቢም የዉሃ መጠኑ እየቀነሰ የሚገኝ ሎጎ ሀይቅም በስጋት ውስጥ ካሉት ይጠቀሳል። ቀድሞ የዉሃዉ ጥልቀት 86 ሜትር ይደርስ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ 50 ሜትር አካባቢ ሆኗል። እናም ሎጎ በከፍተኛ ጉዳት ላይ ነዉ። አንዳንድ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆችም እንዲሁ በአደጋ ላይ መሆናቸዉን ነዉ በፌደራል አካባቢ ጥበቃ ባለስልዕጣን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ለሆኑት አቶ መሃመድ ኢብራሂም የሚናገሩት። በአንፃሩ  መጠናቸው እየጨመረ የመጣ  ሀይቆች በአገሪቱ  አሉ። ለአብነትም ከሳተላይት  የተወሰደ  ምስል እንሚያመለክተው የአቢያታ ሀይቅ የውሃ መጠን  ጨምሯል። ለውሃ  መጠን መጨመሩም በአካባቢው የተሰራው የአካባቢ ጥበቃ ስራ የደለል  ሙላትን ማስቀረቱ በዋነኝነት የሚነሳም  ምክንያት ነው ይላሉ። ስጋት  ያለባቸውን ሀይቆች ልንታደጋቸው የምንችላቸው  የሀይቆቹን አካባቢዎች ተፋሰስ በአካባቢ ጥበቃ ማስተካከልና  ከደለል የፀዳ  ውሃ ብቻ ወደ ሀይቆቹ እንዲገባ በማድረግ  መሆኑን አቶ መሃመድ ተናግረዋል -ዘገባው የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ነው። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
414
ግንባታ ላይ ያሉ 31 ፕሮጄክቶች ሲጠናቀቁ የአዲስ አበባን የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን መቶ በመቶ ይደርሳል ተባለ, .._2012__13. 0 302 227 ; 5; አዲስ አበባ፤ ሰኔ 62004 (ዋኢማ) - ግንባታ ላይ ያሉ 31 የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጄክቶች ሲጠናቀቁ የአዲስ አበባ የመጠጥ ውሃ ሽፋን   መቶ በመቶ እንደሚደርስ የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ ፡፡  የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን  ዋና ሥራ አስኪያጅ  አቶ አሰግድ  ጌታቸው  ለዋልታ  አንደገለጹት  በአሁኑ  ወቅት  የአዲስ አበባ  የመጠጥ  ውሃ ሽፋን  93 በመቶ   መ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከተማዋ በፈጣን  እድገት ላይ  በመሆኗ  በውሃ ፍላጎትና  አቅርቦት መካከል   የ7 በመቶ  ልዩነት  እንደሚታይ የገለጹት ዋና ስራ አስኪያጁ ችግሩን  ለመፍታት 36  ያህል የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በእቅድ  ተይዘው  በ31 የግንባታ ስራው  በ2004 ዓ.ም ተጀምሯል ብለዋል፡፡ መከናወን መጀመራቸውና ከነዚህ ውስጥ 20 ፕሮጀክቶች ከ1ቢሊዮን በላይ በመንግሥት ወጪ እየተሰሩ አንደሚገኙና 10 ፕሮጀክቶች ደግሞ ከአለም ባንክና ከፈረንሳይ የእርዳታ ድርጅት በተገኘ ብድርና እርዳታ እየተካሄደ አንደሚገኝ እንዲሁም አንድ ፕሮጀክት በመንግሥትና በቱርክ የኤግዚም ድጋፍ እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል ፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች እያጋጠመ ያለው የውሃ መቆራረጥ እያጋጠመ ያለው በውሃ ማጠራቀሚያዎች አልፎ አልፎ በሚያጋጥም  የኤሌክትሪክ  መቆራረጥ፣   በከተማ ውስጥ  በሚካሄዱ የመንገድና ሌሎች ግንባታዎች ምክንያት  የውሃ  ቧንቧዎች መቆራረጥ ስለሚያጋጥም መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፍሳሽ  አገልግሎትን  ለማሻሻል  በኮተቤና  አቃቂ ከነበሩት ማጣሪያዎች  በተጨማሪ አንድ ማጣሪያ በ156 ሚሊዮን ዶላር ለመገንባት ዝግጅት ማጠናቀቁን  የገለጹት ዋና  ሥራ አስኪያጁ  ግንባታው  ሲጠናቀቅ  ከሰባት  በመቶ በላይ የሚሆነውን  ፍሳሽ   ለማጣራትና ለማስወገድ  አንደሚያስችል  ተናግረዋል ፡፡),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
415
ባለስልጣኑ የከርሰ ምድር ውሃ ልማትን ለማስፋፋት በዘርፉ ያለውን የሰው ሀይል አቅም በማሳደግ ላይ ይገኛል,   .._2012_. 0 307 230 ; 5; አዲስ አበባ ሐምሌ 172004ዋኢማ- የከርሰ ምድር ውሃ ልማት በሚፈለገው ፍጥነት እንዲጓዝ ለማድረግ በዘርፉ ያለውን የሰው ሀይል አቅም የማሳደግ ስራ እያካሄደ መሆኑን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ። የባለሥልጣኑ የፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ስዩም ብርሃኑ ትናንት ከፈረንሳይ የልማት ደርጅት ጋር በመተባበር በደሳለኝ ሆቴል የተዘጋጀውን የአምስት ቀናት ወርክሾፕ ሲከፍቱ እንደተናገሩት፤ የከርስ ምድር ውሃ ልማትን በሚፈለገው ፍጥነትና ጥራት ለማሳደግ በዘርፉ ያለውን የሰው ሀይል በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እውቀት መገንባት ይገባል። የከርሰ  ምድር  ውሃ ልማትን በሚፈለገው ፍጥነትና ጥራት ለማከናወን ዘርፈ ብዙ ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ጠቁመው፤ ችግሮቹን ለመፍታት ወርክሾፑ የሚኖረው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል። በከተማዋ እየጨመረ ከመጣው የህዝብ ብዛት፣ የኢኮኖሚ እድገትና የመሰረተ ልማት ግንባታ ጋር ተያይዞ የመጣውን የንፁህ ውሃ ፍላጎት ለመሙላት ባለስልጣኑ ከፍተኛ በጀት በመመደብ የከርሰ-ምድርና የገፀ-ምድር ውሃ መገኛዎችን በመለየት መጠነ ሰፊ የጥናትና የውሃ ልማት ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የከርሰ - ምድር ውሃ የማልማቱ ስራ በትግበራ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤  በአቃቂ የውሃ መገኛ ቦታ ላይ ጥልቀታቸው እስከ 500 ሜትር የሚደርሱ ጉድጓዶችን በመቆፈር 223 ሺ ሜትር ኩብ ውሃ በቀን ለማምረት ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። እንዲሁም በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ሌሎች የውሃ መገኛዎች ማለትም በአቃቂ አካባቢው በዌል ፊልድ ሁለትና ሶስት ተብለው በተለዩ አካባቢዎች 140 ሺ ሜትር ኩብ ውሃ በቀን ለማምረት ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን ተናግረዋል። በሰበታ፣ በለገዳዲና በአያት አካባቢዎች የከርሰ ምድር ውሃ ጥናት በስፋት በመከናወን ላይ ሲሆን፤ የጥናቱ ውጤት እንደተጠናቀቀ የጉድጓድ ቁፋሮ ስራ ለማከናወን እቅድ ተይዟል ብለዋል። በተጨማሪም ከአለም ባንክ በተገኘ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አስር የከርሰ ምድር የውሃ ጉድጓዶችን ለመቆፈር ከአሜሪካው ላየን ኢንተርናሽናል ጋር የኮንትራት ውል መፈረሙን ተናግረዋል፡፡በመሆኑም የከርሰ ምድር ውሃ ልማቱን በሚፈለገው ፍጥነትና ጥራት ለማስኬድ በዘርፉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን መፍታት ይገባል በማለት ገልፀዋል። ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚሰጠው ስልጠና የተቃና እንዲሆን ተመኝተው፤ በከተማው የሚካሄዱ የከርሰ ምድር የውሃ ልማት እቅድን ከማሳካት አንፃር ጉልህ ሚና ያለው በመሆኑ በስልጠናው በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር በማምጣት በዘርፉ ላይ የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲወጡ አሳስበዋል። በዎርክሾፑ ላይ ከተለያዩ  ከውሃ ጉድጓድ  ቁፋሮ ጋር  የተገናኘ ሥራ የሚሰሩ ከሃምሳ  በላይ የመንግሥትና የግል ኩባንያ ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎችና አማካሪዎች  መገኘታቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።  ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
416
በአዳማ ከተማ ላለፉት ቀናት የተቋረጠው የንፁህ መጠጥ ውሀ ችግር እስከ ነገ ምሽት ይፈታል ተባለ, - ; .._2012_. 0 260 197 ; 5; አዲስአበባ፤ መስከረም42005 (ዋኢማ) - በአዳማ ከተማ ላለፉት ጥቂት ቀናት የተቋረጠው የንፁህ መጠጥ ውሀ ችግር እስከ ነገ ምሽት ድረስ የክልሉ የውሀና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ። በአዳማ ከተማ  የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት ከተቋረጠ አስራ ስምንት ቀናት ሆኖታል። የከተማ አስተዳደሩና የውሀና ፍሳሽ ፅህፈት ቤት ችግሩ የተከሰተው ከቆቃ ወደ አዳማ የሚመጣው የውሀ መስመር ላይ በደረሰ አደጋ ነው ብሏል። ከዚህ በፊት የውሀ መቆራረጥ ሲያጋጥም አስተዳደሩ በፍጥነት ችግሮቹን ለመፍታት ጥረቶችን ሲያደርግ የቆየ ቢሆንም ፥ የአሁኑ ችግር ከበድ ያለ መሆኑ ለቀናት እንዲቆይ እንዳደረገው ነው ሀላፊዎቹ የተናገሩት። ችግሩን ለመፍታትም ርብርብ እየተደረገ መሆኑንና ፥ በአሁኑ ጊዜም በቦቲና በሌሎች መንገዶች ለነዋሪው ውሀ እየቀረበ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። የከተማው ነዋሪ ችግሩን ለመፍታት እየተደረገ ያለውን ጥረት በማየት እያሳየ ላለው እገዛና ትእግስት ምስጋናችንን እናቀርባለንም ማለታቸውን ፋና ዘግቧል። ከችግሩ ስፋትና መልሶ ለመጠገን የሚደረገውን ጥረት ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ተደጋጋሞ በሚደርስ የጎርፍ አደጋ ሌላው ስራውን በፍጥነት እንዳይጠናቀቅ አድርጎታል። በአሁኑ ጊዜ ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝና ከ48 ሰአት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ መፍትሄ እንደሚያገኝ ያላቸውን ተስፋ የገለጹት ደግሞ በውሀና ኢነርጂ ሚንስቴር የውሃ ሳኒቴሽን ዳይሬክተር አቶ ዮሀንስ ገብረመድህን መግለጻቸውን ፋና ዘግቧል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
417
 ድርጅቱ ለመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ 38 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር መደቤ ። በባሌ ዞን ዶዶላ ከተማና አካባቢው የሚታየውን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተያዘው አመት 38 ሚሊየን 700ሺ ብር በጀት መድቦ እንቅስቃሴ መጀመሩን የኢትዮ-ጣሊያን ልማት ድርጅት አስታወቄ ። በድርጅቱ የአርሲ ባሌ ገጠር ልማት ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ዩሴፍ ፈረዴ ዛሬ እንደገለጹት በከተማውና አካባቢው 11 ቀበሌዎች የሚታየውን የመጠጥ ውሃ እጥረት ለመቅረፍ ድርጅቱ በአሁኑ ጊዜ ጥናቱን ጨርሶ ግንባታ ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቅቋል ። እንዴ ስራ አስኪያጁ ገለጻ በጀቱ እንደተለቀቄ የፕሮጀክቱ የቧንቧ መዘርጋት ፣ የውሃ ማጠራቀሚያዎች ተከላ ፣ የውሃ ማደያዎች ግንባታና የምንጭ ማጎልበት ስራዎች ይካሄዳሉ ። የፕሮጀክቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ የዶዶላ ከተማ ቸምሮ በአካባቢው 11 ቀበሌዎች የሚገኙ 29 ሺ 298 ነዋሪዎች በበቂ ሁኔታ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል ። የዶዶላ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች በንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት ሲቸገሩ መቆየታቸው በተደጋጋሚ መገለጹ ይታወሳል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
418
9 ሚሊዮን ሰዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ አገኙ, - ; .._2014 . 0 261 196 ; 5; አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19 2006 (ዋኢማ) - በተጠናቀቀው ባጀት ዓመት በመላው አገሪቱ ከ 9 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸውን የውሃ ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። - ; በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢዜአ እንደገለጹት ሚኒስቴሩ በአገር አቀፍ ደረጃ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማዳረስ ባደረገው ጥረት ባለፈው አመት ከነበረበት 68 በመቶ በአሁኑ ወቅት 76 ነጥብ 6 በመቶ አድርሷል። - ; ሚኒስቴሩ በባጀት ዓመቱ በአገር አቀፍ ደረጃ 103 ከተሞችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቀሚ ለማድረግ አቅዶ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን ያብራሩት ዳይሬክተሩ ፣በአዲስ አበባ የሚካሄደወን ማስፋፊያን ጨምሮ በ78 ከተሞች የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተከናውኗል። - ; በገጠር አካባቢዎችም አቅዶ  27 ሺየንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት አጠናቆ ለአገልግሎት አብቅቷል። - ; በአጠቃላይ በባጀት ዓመቱ በገጠርና በከተማ ተገንብተው በተጠናቀቁ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ከ 9 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ተጠቃሚ ማድረጋቸወን አቶ ብዙነህ አመልክተዋል። - ; ለፕሮጀክቶቹ ማስፈፀሚያ ጥቅም ላይ የዋለው 5 ቢሊዮን ብር በመንግስትና በዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች በጋራ የተሸፈነ መሆኑንም  ተናግረዋል። - ; የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ከሆኑት ከተሞች መካከል ደበሶ፣ሊሙገነት፣አምቦ፣መቂ፣ቢሸፍቱ፣ሁሩታና ቡራዩ ይጠቀሳሉ (ኢዜአ)),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
419
ባለሥልጣኑ የአምስት ንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ግንባታ እያካሄደ ነው, - ; .._2014. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ ፤ጳጉሜን 3 2006 (ዋኢማ) - እያደገ የመጣውን የአዲስ አበባ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፍላጎት ለማሟላት በ5 ቢሊዮን ብር ወጪ አምስት የውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ እያካሄደ መሆኑን የከተማው ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን አስታወቀ። በባለሥልጣኑ የውሃ አቅርቦትና ሥርጭት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈቃዱ ዘለቀ ለዋልታ እንደገለጹት ፕሮጄክቶቹ አሁን ካለው የውሃ አቅርቦት በተጨማሪ በቀን 249 ሺ ሜትር ኩብ ውሃ ለማቅረብ የሚያስችሉ ናቸው። - ; ፕሮጀክቶቹ ከፊታችን መስከረም ጀምሮ እስከ ግንቦት ወር ድረስ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት የሚጀምሩ ሲሆን ይህም አሁን በከተማው በቀን የሚሠራጨውን 350 ሺ ሜትር ኩብ ውሃ ወደ 599ሺ ሜትር ኩብ እንደሚያሳድገው አስረድተዋል ። እንደ አቶ ፈቃዱ ገለጻ ከፕሮጀክቶቹ መካከል በቀን 70ሺ ሜትር ኩብ ውሃ የማምረት አቅም ያለው የአቃቂ ከርሰ ምድርና ጥልቅ ውሃ ስሪ ‘ኤ’ ተብሎ የሚጠራው ፕሮጀክት በመጪው መስከረም ወር አገልግሎት መሥጠት የሚጀምር ሲሆን ሌላኛውና 70ሺሜትር ኩብ ማምረት የሚችለው የአቃቂ ከርሰ ምድርና ጥልቅ ውሃ ስሪ ‘ቢ’ የተባለው ፕሮጀክት ደግሞ በየካቲት ወር ለአገልግሎት ይበቃል - ; በተጨማሪም የለገዳዲ የከርሰ ምድር ውሃ ላይ የማስፋፊያ ሥራ በማካሄድና የድሬ ግድብን በማሻሻል እንዲሁም የምዕራፍ ሁለት የአቃቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክትን በ2007 ዓም በማጠናቀቅ በአጠቃላይ 88ሺ ሜትር ኩብ ውሃ በአዲስ አበባ ከተማ የማሠራጨት አቅም ይፈጠራል ብለዋል - ; በከተማው የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች 20 ጥልቅ ጉድጓዶችን በመቆፈር በቀን 21ሺ ሜትር ኩብ ውሃ ለማምረት ባለሥልጣኑ ጥረት እያደረገ ነው ያሉት አቶ ፈቃዱ እስካሁን አራት ጉድጓዶች መቆፈራቸውን ገልጸዋል። ከውሃ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ችግሮች ሲያጋጥሙ በህብረተሰቡ ጥቆማ ማስተካከያዎች እንደሚደረጉ የጠቆሙት አቶ ፈቃዱ ለህብረተሰቡ ያለውን ተደራሽነት ይበልጥ ለማሻሻልም ባለስልጣኑ የራሱን የስልክ ጥሪ ማዕከል ለመቋቋም በዝግጅት ላይ  መሆኑን ገልጸዋል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
420
ባለፉት 4 ዓመታት 31 ሚሊዮን ህዝብ የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ሆኗል , - 1.3; .._2014. 0 262 197 ; 5; አዲስ አበባ ፣ መስከረም 28 2007 (ዋኢማ) - በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ አራት ዓመታት ውስጥ በመላው አገሪቱ ከ31 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ መሆኑን የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ። በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ እንደገለጹት  በመጠጥ ውኃ አቅርቦት ጥረቱ ከተማና ገጠርን ጨምሮ አገራዊ የንጹህና ዘላቂ መጠጥ ውኃ ሽፋኑን 76 ነጥብ 7 በመቶ እንዲደርስ እንዳደረገው ገልጸዋል። ከተቀመጠው ግብ ጋር ሲነፃፃርም በገጠር 103 ነጥብ 2 በመቶ በከተማ 123 ነጥብ 1 በመቶ እንዲሁም ከጠቅላላው 105 በመቶ ማሳካት መቻሉን አመልክተዋል። በእቅድ ዘመኑ ውስጥ በ1 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ በነፍስ ወከፍ በቀን 15 ሊትር ውኃና በከተማ በግማሽ ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ በነፍስ ወከፍ በቀን 20 ሊትር ውኃ ለማቅረብ እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም በመላው አገሪቱ ከ10 ሚሊዮን በላይ ህዝብን የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።   ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
421
ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሆኑ , - ; .._2014_22_14. 0 257 193 ; 5; አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 122007 (ዋኢማ) - ባለፉት አራት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ትግበራ ዓመታት ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸውን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ እንደገለጹት የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል 28 ሚሊየን በላይ የሚሆኑት በገጠር የሚኖሩ ሲሆኑ ቀሪዎቹና ከ3 ነጥብ 24 ሚሊየን በላይ የሚሆኑት ደግሞ በከተማ የሚኖሩ ናቸው። ባለፉት አራት ዓመታት ባጠቃላይ 29 ነጥብ 78 ሚሊየን ያህል ዜጎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ የእቅዱን 105% ማሳካት መቻሉን ተናገረዋል።    አቶ ብዙነህ አያይዘው እንደገለጹት ባለፉት አራት ዓመታት በገጠር 76,354 እንዲሁም በከተማ 214 የውሃ ተቋማት ግንባታ፣ የማስፋፊያና የመልሶ ማቋቋም ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ የመሳሪያዎች ፣ የተቋራጮችና ባለሙያዎች እጥረት እንዲሁም በየደረጃው ያሉ የአስፈፃሚ አካላት የክትትል፣ ግምገማና ግብረ መልስ አቅም ውስንነት በዕቅዱ ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ችግሮች መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመኑ ማብቂያ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቱን በገጠር በነፍስ ወከፍ በቀን 15 ሊትር በከተማ ደግሞ 20 ሊትር ለማድረስ የተቀመጠውን ግብ  ለማሳከት ሚኒስቴሩ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
422
በከተማዋ በ5 ነጥብ6 ቢሊዮን ብር ወጪ የውሃ ፕሮጀክቶች እየተካሄዱ ነው, - ; .._2015_10. 0 250 196 ; 5; አዲስ አበባ፣ ጥር 2 2007 (ዋኢማ) - የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የከተማዋን የውሃ አቅርቦት ለማሳደግ ከ5ነጥብ6 ቢሊዮን ብር ወጪ በመመደብ እየሰራ ነው። - ; ባለስልጣኑ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ጋር በመተባበር በውሃ አቅርቦትና ጥራት ላይ በሚከናወኑ ተግባራትና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከኅብረተሰቡ ጋር ውይይት አካሂዷል። - ; የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አወቀ ኃይለማሪም በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ የከተማዋን የውሃ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ባለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ በመሥራት ላይ ይገኛል። በዚህም ችግሩን ለመፍታት የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ዕቅድ ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። - ; ከተማዋ ያጋጠማትን ጊዜያዊ ችግር ለመፍታት በከተማዋ በተለይ ዳገታማ በሆኑ ውሃ የማይደርስባቸው አምስት ክፍለ ከተሞች በ42 ማጠራቀሚያዎች 300ሺህ ህዝብ ተጠቃሚ አድርጓል። በአቃቂ ተጨማሪ ውሃ ጉድጓድ የመቆፈር፣ የድሬና የለገዳዲ ግድቦችን ማስፋፋት ሥራ መከናወኑንም  አቶ አወቀ አመልክተዋል። የድሬ ግድብ አቅምም ከ30ሺህ ሜትር ኩብ ውሃ በሁለት ዕጥፍ ማደጉንም ተናግረዋል። - ; የለገዳዲ ግድብ በቀን 165 ሺህ ኪዩብ ሜትር ውሃ የማጣራት አቅም እንደነበረው አስታውሰው፣ አሁን በተደረገው ማስፋፊያ አቅሙ ወደ 195ሺህ ኪዩብ ሜትር  ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። በዚህም አቅርቦቱን በማሻሻል በዋነኝነት የምሥራቅ አካባቢ ቦሌ፣ የካ፣ ጉለሌ፣ልደታና አራዳ ክፍለ ከተሞችን በከፊል እስከ 24 ሰዓት በሚደርስ የውሃ አገልግሎት ተጠቅመዋል። በከተማዋ የውሃ እጥረት የተፈጠረው በአገሪቱ ብሎም በከተማዋ በሚታየው ፈጣን ዕድገት አቅርቦትና ፍላጎትን ባለመጣጣማቸው መሆኑን ገልፀው፣ችግሩን ለመፍታት የተጀመሩት ተግባራት ተጠናከረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። - ; ዕጥረቱን የሚያባብሰው የመሰረተ ልማት ተቋማት ቅንጅት ማነስናየኃይል ማነስ ተግዳሮቶች እንደነበሩ ገልጸው፣ ችግሩን ለመፍታት በአጋርነት ተቀናጅቶ መሥራት እንደሚገባ አስታወቀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ በየነ በበኩላቸው አስተዳደሩ የውሃ አቅርቦትን ችግር ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት ለማሳወቅና ኅብረተሰቡ በአገልግሎቱ ዙሪያ ያለውን አስተያየት በመሰብሰብ ምላሽ እንዲሰጠው ለማስቻል ያለመ ነው። - ; የከተማዋ አስተዳደር ለውሃ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከፍተኛ የሆነ በጀት መድቦ የኅብረተሰቡን የውሃ ችግር ለመፍታትና ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር አልሞ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አመልክተዋል። - ; በውይይቱም ላይ ውሃ ሲፈስ ጥቆማ ቢደረግም ቶሎ መጥቶ የመጠገን ሁኔታ አይታይም፣ የመልካም አስተዳደር ችግር መኖር የውሃ ስርጭት ሚዛናዊ ያለመሆን ወሃን ለማዳረስ የተቀመጡ ቦቲዎች ለመሙላት፣ ክትትል አይደረግምና ውሃ ወደ ከፍታ እንዳይወጣ በተለይ በኮምደሚኒየም አካባቢ የግፊት ዕጥረት መኖሩ የመሳሰሉት ከተሳታፊዎች ጥያቄ ቀርበው በባለስልጣኑ ምላሽ ተሰጥቶበታል። (ኢዜአ)),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
423
የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ሙሉ በሙሉ ይሳካል- የሚኒስቴሩ, - ; .._2015_14. 0 260 172 ; 5; አዲስ አበባ ፣ ጥር 6 2007 (ዋኢማ) - የአገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ሙሉ በሙሉ እንደሚሳካ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ - ; የሚኒስቴሩ የኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ እንደገለፁት በ2006 በጀት ዓመት መጨረሻ ሀገር አቀፉ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት 76.7 በመቶ ደርሷል። - ; አቅርቦቱ በተያዘው የበጀት ዓመት መጨረሻ 80.83 የሚደርስ ሲሆን በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ውስጥ ሽፋኑን ሙሉ በመሉ ለማሳካተ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ - ; የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦቱን ለማሟላት በየአመቱ ከአምስት እስከ ሰባት ቢሊዮን ብር በጀት እየተመደበ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታና ማስፋፊያ እንደሚካሄድ ኃላፊው አስረድተዋል፡፡ - ; እንደ አቶ ብዙነህ ገለጻ በ2003 ዓም በተደረገ ቆጠራ በአገሪቱ ያሉት አጠቃላይ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ብዛት 94ሺህ 400 የነበር ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ቁጥሩ 161ሺህ 813 ደርሷል፡፡ - ; ተጨማሪ የውሃ ተቋማትን ለመገንባት ጥረት እየተደረገ ሲሆን በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል መሳሪያዎች እጥረት እንዲሁም የኮንትራክተሮችና አማካሪዎች አቅም ውስንነት በዘርፉ የተጋረጡ ተግዳሮቶች እንደሆኑ ኃላፊው ተናግረዋል። - ; ተግዳሮቶቹን ለመፍታትም በአገሪቱ ካሉ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችና የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ባለሙያዎችን ለማፍራት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየሰራ መሆኑን አቶ ብዙነህ አስረድተዋል፡፡),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
424
የድሬና የለገዳዲ ግድብ የውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ , .._2015. 0 263 197 ; 5; አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7 2007 (ዋኢማ) - የድሬና የለገዳዲ ግድብ የውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። የአዲስ አበባ ከተማን የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር በከፍተኛ ደረጃ ለማቃለል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አራት ፕሮጀክቶችን ገቢራዊ እያደረገ ይገኛል። ከእነዚህ ውስጥም በዛሬው ዕለት በ682 ሚሊዮን ብር ማሰፋፊያ ግንባታ የተከናውነባቸው የድሬ ግድብና የለገዳዲ የውሃ ማጣሪያ ጣቢያዎች ተመርቀዋል። የድሬ ግድብ ከዚህ ቀደም ይይዝ ከነበረው 30 ሺህ ሜትር ኩብ ውሃ በማስፋፋያው ወደ 60 ሺህ ሜትር ኩብ ውሃ የመያዝ አቅሙ እንዲያድግ ተደርጓል። 165 ሺህ ሜትር ኩብ ውሃ ያጣራ የነበረው የለገዳዲ የውሃ ማጣሪያ ጣቢያም የማስፋፋያ ፕሮጀክቱ አቅሙ 195 ሺህ ሜትር ኩብ ደርሷል። የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ በመንግስት፣ በአለም ባንክ እና በፈረንሳይ የብድር ተቋም ኤ ኤፍ ዲ በተገኝ የረጅም ጊዜ ብድር ነው የተከናወነው። የከተማው ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ከማድረጉም በተጨማሪ የመስመር ዝርጋታዎችን በራስ አቅም ለማከናወን ተችሏል  ነው ያሉት የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ። የመዲናዋን የውሃ አቅርቦት እጥረት በአሰተማማኝ ደረጃ ለመቅረፍም በአስተዳደሩ የተጀመሩ የውሃ ፕሮጀክቶች እንዲፋጠኑ ይደረጋል ብለዋል ከንቲባው። የከተማው ነዋሪ የተከሰተውን የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት በተለያዩ መንገዶች በመቋቋም ላሳየው ትዕግስትም ምስጋና አቅርበዋል። አሁን ወደ ማሰራጫ መስመር የሚገባው ውሃም የመዲናዋን ሰሜንና ሰሜን ምስራቅ አካባቢ ነዋሪዎች የውሃ አቅርቦት የሚያሻሽል ይሆናል። በሃገሪቱ እየተመዘገበ ካለው ፈጣን ዕድገት አኳያ የአዲስ አበባ ከተማ በአጭር ጊዜ ውሰጥ እየሰፋች መታለች፣ ይህም ውሃን ጨምሮ የተለያዩ ችግሮች በመዲናዋ እንዲፈጠሩ አድርጓል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን። እነዚህ ችገሮች ለመቅረፍም የጋራ ርብርብ እንደሚጠይቅ እና መንግስትም በከተማው የሚስተዋለው የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረትን ለመቅረፍ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ነው የተናገሩት። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ እንደተናገሩት የአዲስ አበባ አሰተዳደር የውሃ መገኛዎችን በማልማት የውሃ አጥረቱ ለማቃለል  የሚያከናውናቸው ተግባራት እንዳሉ ሆነው በተጨማሪም የአግልግሎት አሰጣጡን ማሻሻል ይጠበቅበታል። (ኤፍ.ቢ.ሲ)),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
425
ኢትዮጵያ በንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ አሳካች , - ; .._2015_23. 0 281 210 ; 5; አዲስ አበባ፤ መጋቢት 142007(ዋኢማ)-- ኅብረተሰቡን የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ለማድረግ የተቀመጠውን የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ ማሳካቷ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። በተያዘው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ የሚጠናቀቀው በንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ዘርፍ የምዕተ ዓመቱ የልማት ግብ አቅርቦቱን በግማሽ ማሳደግ እንደሆነ የመንግሥታቱ ድርጅት መረጃ ያመለክታል። ሚኒስትሩ እንደሚሉት አገሪቱ ለንፁህ መጠጥ ውኃና ሳኒቴሽን አገልግሎት ትኩረት በመስጥት የንፁህ መጠጥ ውኃ ተቋማትን ተደራሽ ማድረግ በመቻሏ በመስኩ የተቀመጠውን የምዕ ዓመቱን ግብ አሳክታለች። ሚኒስቴሩ 22ኛው ዓለም አቀፍ የውኃ ቀንን ውኃና ዘላቂ ልማት በሚል መሪ ቃል ትናንት በተለያዩ ዝግጅቶች ያከበረ ሲሆን በዘርፉ የልማት ሥራዎች በመስራት ሞዴል ለሆኑ ወረዳዎችና ተቋማት እውቅና ሰጥቷል። ተሸላሚዎቹ ከ9 ክልሎችና ከሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች በራስ አገዝ የመጠጥ ውኃ መርሃ ግብር፣ በውኃ፣ በመስኖ እና በኢነርጂ ዘርፍ አፈፃጸም ውጤታማ የሆኑ ናቸው። ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ እንደገለጹት በገጠር ያለው የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት 75 ነጥብ 5 በመቶ የደረሰ ሲሆን በከተማ ደግሞ 84 ነጥብ 2 በመቶ ማድረስ ተችሏል ። በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱም የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት 29 ነጥብ 8 ሚሊዮን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ በአራት ዓመት ውስጥ 31 ነጥብ 3 ሚሊዮን ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል ። ከ1984 ዓ.ም ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ከፍተኛ ትኩረት በ2006 በጀት ዓመት መጨረሻ የአገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ወደ 76 ነጥብ 7 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ አስታውቀዋል ። ለዚህ ስኬትም የአገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦች ሕዝቦች፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተዋጽኦ ተጠቃሽ መሆኑን አስረድተዋል ። ከ23 ዓመታት በፊት የአገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት 19 ነጥብ 2 በመቶ እንደነበር ከሚኒስቴሩ የተገኘ መረጃ ያሳያል። (ኢዜአ) );
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
426
በአገሪቱ የንጹህ ውሃ መጠጥ ሽፋን 79 በመቶ መድረሱን ሚኒስቴሩ አስታወቀ ። , - ; .._2015 24. 0 ; 5; አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 162007(ዋኢማ)-የአገሪቱ አጠቃላይ የንጹህ ውሃ መጠጥ ሽፋን 79 በመቶ  መድረሱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር  አስታወቀ ። - ; የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ከበደ ገርባ ለዋልታ እንደገለጹት በአገሪቱ የገጠርና ከተማ አካባቢዎች የንጹህ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መሠረት በተካሄደው እንቅስቃሴ የአገሪቱ አጠቃላይ የንጹህ ውሃ ሽፋን 79 በመቶ ደርሷል ብለዋል። - ; ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የአገሪቱን የንጹህ ውሃ ፍላጎት ለሟሟላት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አስፈላጊውን በጀት በመመደብ ሥራዎችን እያካሄደ ነው ያሉት አቶ ከበደ  በአሁኑ  ወቅት  የከተማ የንጹህ ውሃ መጠጥ ሽፋን 86 በመቶ የገጠር የንጹህ መጠጥ ሽፋን 78 በመቶ መሆኑን  ገልጸዋል። - ; ባለፉት አራት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዓመታት ሚኒስቴር መሥሪያቤቱ 32ነጥብ5 ሚሊዮን  ሚሊዮን  ህዝብ  የንጹህ ውሃ ተጠቃሚ  ለማድረግ ዕቅድ ተይዞ የአገሪቱ የንጹህ ውሃ ሽፋን በየዓመቱ 8 በመቶ ዕድገትበማሳየት ከ33 ሚሊዮን በላይ ህዝብን ተጠቃሚ በማድረግ  በሚሊኒየም የልማት ግብ በመጠጥ ውሃና ንጽህና የተቀመጠውን ግብ ማሳካት መቻሉን አስረድተዋል ። - ; በዘንድሮ የበጀት ዓመት ሚኒስቴሩ በመላው አገሪቱ 49ሺ አዳዲስ የመጠጥ ውሃ ተቋማትን በመገንባት 15ሚሊዮን ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርግ ዕቅድን ማውጣቱን የገለጹት አቶ ከበደ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 9ሺ የሚሆኑት የመጠጥ ውሃ ተቋማት አገልግሎት ጀምረው 3ነጥብ 6  ሚሊዮን ህዝብን የንጹህ ውሃ  ተጠቃሚ አድርገዋል ብለዋል ። - ; በኢትዮጵያ 80 በመቶ የሚሆነው የመጠጥ ውሃ  ከከርሰ ምድር  እንደሚገኝና  በገጠር የአንድ ሰው  የቀን አማካኝ  የውሃ ፍጆታ 15ሊተር ሲሆን በከተማ 20 ሊትር  መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል ።   ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
427
የኢትዮጵያ የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ከ71 በመቶ በላይ ደረሰ , - ; .._2014. 0 262 197 ; 5; አዲስ አበባ ፤ ግንቦት 26 2006 (ዋኢማ) - ኢትዮጵያ በንጹህ መጠጥ ውሃ  አቅርቦት ሽፋን በምእተ ዓመቱ የተቀመጠውን ግብ ከአንድ ዓመት ቀደም ብላ ማሳካት መቻልዋን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሰሜን ጎንደር ለዳባትና ወቅን ከተሞች በ87 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው ዘላቂ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀከት ተመርቋል። - ; የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ ዓለማየሁ ተገኑ በምረቃው ወቀት እንደተናገሩት በምእተ ዓመቱ የተቀመጠውን 70 በመቶ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋን ሀገሪቱ ቀደም ብላ ማሳካት ችላለች። ከ23 ዓመታት በፊት 17 በመቶ የነበረው ሀገራዊ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋን በአሁኑ ወቅት ከ71 በመቶ በላይ ማድረስ መቻሉንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል። - ; በዚህም ከ60 ሚሊዮን በላይ የሚሆነውን ህዝብ በአነስተኛ፣ በመካከለኛና በከፍተኛ ቴክኖሎጂ በተገነቡ የውሃ ተቋማት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመኑም የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋኑን  በገጠር 98 በመቶ፣ በከተማ መቶ በመቶ እንዲሁም ሀገራዊ ሽፋኑን ደግሞ 98 በመቶ ለማድረስ የተጠናከረ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነም ገልጸዋል። - ; የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርእሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በበኩላቸው በክልሉ ከፍተኛ በጀት ከሚመደብላቸው የልማት ፕሮጀክቶች የንጹህ መጠጥ ውሃ አንዱ መሆኑን ገልጸው በዚህ ዓመትም ከ1ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ክልሉ መመደቡን ተናግረዋል። - ; የሁለቱ ከተሞች የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ በክልልና በፌደራል መንግስት የጋራ ትብብር የተከናወነ መሆኑን ጠቁመው ህብረተሰቡ ለተቋማቱ ተገቢውን ጥበቃና ክብካቤ በማድረግ በአግባቡ እንዲጠቀምባቸው አሳስበዋል። የዳባት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰጠኝ አዲሱ የተገነቡት የውሃ ተቋማት ለቀጣዮቹ 20 ዓመታት ቁጥሩ ከሃምሳ ሺ በላይ ለሚሆነው ለሁለቱ ከተሞች ነዋሪዎች አስተማማኝ የንጹህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ማቅረብ ያስችላል ብለዋል። - ; ወይዘሮ ማናስብ አሰፋና ወይዘሮ ጥላዬ የኋላእሸት የከተማው ሴቶችና ህጻናት ውሃ ፍለጋ 10 ኪሎ ሜትር በመጓዝ ከፍተኛ እንግልትና ስቃይ ማሳለፋቸውን ገልጸው መንግስት ከፍተኛ ወጪ አውጥቶ ዘላቂ መፍትሄ በመስጠቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
428
ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ የ327 ሚሊዮን ዶላር ብድር ተፈራረሙ, .._2016. 0 260 195 ; 5; አዲስ አበባ፣ጥር 25 2008 (ዋኢማ) - ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ ለመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ለመሰረታዊ አገልግሎቶች ማሻሻያ የሚውል የ327 ሚሊዮን ዶላር ብድር ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ የብድር ስምምነቱ ዛሬ በገንዘብና የኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር አዳራሽ ሲፈረም ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አህመድ ሺዴ እንደተናገሩት የተገኘው ገንዘብ ሁለት የብድር ስምምነቶችን ያቀፈ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ አንደኛው የብድር ስምምነት መሰረታዊ አገልግሎቶችን በጥራትና በፍትሃዊነት ለማዳረስ እንዲረዳ በበባንኩ የተፈቀደ 251 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በአራት ከተሞች ለሚከናወን የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ለሳኒቴሽን አገልግሎት የሚውል 76 ነጥብ አንድ ሚሊዮን ዶላር መሆኑን ሚኒስቴር ዴኤታው ገልፀዋል፡፡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ የማድረግ፣ አገልግሎት አሰጣጡን ፍትሃዊና ቀልጣፋ የማድረጉ ሥራ በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች እስከ ወረዳ ድረስ በማውረድ የሚሰራ ይሆናል ተብሏል፡፡ የውሃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን ሥራው ደግሞ በአራት የክልል ከተሞች ይከናወናል፡፡ እነዚህም ቢቸና፣አድዋ፣አዳማና ጎዴ ከተሞች መሆናቸው ተመልክተቷል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ተወካይ ዶክተር ጆሴፊን ኒጉሬ በበኩላቸው ኢትዮጵያ እአአ ከ2006 ጀምሮ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማሳለጥና ለማስፋፋት የምታደርገውን ጥረት እየደገፈ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ማፋጠንና ፍትሃዊ ማድረግ ለድህነት ቅነሳ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ጠቁመው ስምምነቱም ይህንን ለማጠናከር የሚረዳ ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማሳደግና መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማሻሻል ለነደፈችው መርሃ ግብር ባንኩ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ዶክተር ኒጉሬ ገልፀዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማካናወን ያስቀመጠችው ግብ ዕውን ለማድረግ ባንኩ የበኩሉን ድጋፍ በማድረግ ለዕቅዱ ስኬት ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚሰለፍ ነው የተናገሩት፡፡ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ ግንኙነታቸውን በማጠናከር ፀረ ድህነት ትግሉ ግቡን እንዲመታ በቅርበት እንደሚሰሩ በፊርማ ስምምነቱ ላይ ተገልጧል፡፡),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
429
የጋምቤላ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ስልሳ አምስት በመቶ ደረሰ, .._2013. 0 260 195 ; 5; ጋምቤላ ፣ ታህሳስ 72006 (ዋኢማ) - የጋምቤላ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ከአርባ በመቶ ወደ ስልሳ አምስት በመቶ መድረሱን የከተማው ውሃ አገልግሎትና ፍሳሽ ኤጀንሲ አስታወቀ። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አቡላ ኡዳንጊ የክልሉ መንግስት በ2 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር ውጪ የተከላቸው የውሃ ፓምፖች በከተማው እየጨመረ ላለው የውሃ አቅርቦት ምክንያት አንደሆነ ገልጸዋል ። የከተማውን ነዋሪ ህዝብ መጠጥ ውሃ ሽፋን ሙሉ በሙሉ ለማዳረስ ኤጀንሲው የማስፈፀም አቅሙን በሙሉ እየተጠቀመ መሆኑን ነው አቶ አቡላ የገለፁት። ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘው እንደገለጹት ኤጀንሲ በ2006 ዓመት በያዘው እቅድ በከተማው የሚገኙትን የመጠጥ ውሃ ደንበኞች ቁጥር ከሁለት ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና ወደ ሶስት ሺህ አምስት መቶ ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል። ኤጀንሲው በበጀት አመቱም ከሶስት ሚሊየን ብር በላይ ከተጠቃሚዎች ለመሰብሰብ አቅዶ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ የዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘገባ ያመለክታል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
430
በ2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ወጪ የመገጭ የመስኖና መጠጥ ውሃ ግድብ ግንባታ ተጀመረ, .._2013. 0 260 195 ; 5; አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 17 2006 (ዋኢማ) -ከ2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የሚደረግበት የመገጭ የመስኖና መጠጥ ውሃ ግድብ ግንባታ ተጀመረ። ከጎንደር ከተማ በቅርብ ርቀት በመገጭ ወንዝ ላይ የሚገነባው ግድብ ሲጠናቀቅ አንድ ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ የማጠራቀም አቅም ይኖረዋል። የፕሮጄክቱ ኃላፊ አቶ አጎናፍር ዘውዴ እንደተናገሩት፣ ግድቡ 17 ሺህ ሄክታር መሬት በመስኖ ማልማት የሚያስችል ነው። ከዚህ በተጨማሪም 300 ሺ ለደረሰው የጎንደር ከተማ ህዝብ ለመጪዎቹ 100 ዓመታት አስተማማኝ የመጠጥ ውሃ ማቅረብ ያስችላል። በኢትዮጵያ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ባለቤትነት የሚገነባው ይህው ግድብ 76 ሜትር ከፍታና 890 ሜትር ርዝመት አለው። የግድቡ ስራ መጀመር ከ500 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን የግንባታው ወጪም በመንግስት የሚሸፈን መሆኑን ኤፍ.ቢ.ሲ ዘገባ ያስረዳል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
431
9 ሚሊዮን ሰዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ አገኙ, - ; .._2014 . 0 261 196 ; 5; አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 19 2006 (ዋኢማ) - በተጠናቀቀው ባጀት ዓመት በመላው አገሪቱ ከ 9 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸውን የውሃ ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። - ; በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢዜአ እንደገለጹት ሚኒስቴሩ በአገር አቀፍ ደረጃ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማዳረስ ባደረገው ጥረት ባለፈው አመት ከነበረበት 68 በመቶ በአሁኑ ወቅት 76 ነጥብ 6 በመቶ አድርሷል። - ; ሚኒስቴሩ በባጀት ዓመቱ በአገር አቀፍ ደረጃ 103 ከተሞችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቀሚ ለማድረግ አቅዶ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን ያብራሩት ዳይሬክተሩ ፣በአዲስ አበባ የሚካሄደወን ማስፋፊያን ጨምሮ በ78 ከተሞች የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተከናውኗል። - ; በገጠር አካባቢዎችም አቅዶ  27 ሺየንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት አጠናቆ ለአገልግሎት አብቅቷል። - ; በአጠቃላይ በባጀት ዓመቱ በገጠርና በከተማ ተገንብተው በተጠናቀቁ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ከ 9 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ተጠቃሚ ማድረጋቸወን አቶ ብዙነህ አመልክተዋል። - ; ለፕሮጀክቶቹ ማስፈፀሚያ ጥቅም ላይ የዋለው 5 ቢሊዮን ብር በመንግስትና በዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች በጋራ የተሸፈነ መሆኑንም  ተናግረዋል። - ; የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ከሆኑት ከተሞች መካከል ደበሶ፣ሊሙገነት፣አምቦ፣መቂ፣ቢሸፍቱ፣ሁሩታና ቡራዩ ይጠቀሳሉ (ኢዜአ)),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
432
ባለሥልጣኑ የአምስት ንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ግንባታ እያካሄደ ነው, - ; .._2014. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ ፤ጳጉሜን 3 2006 (ዋኢማ) - እያደገ የመጣውን የአዲስ አበባ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፍላጎት ለማሟላት በ5 ቢሊዮን ብር ወጪ አምስት የውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ እያካሄደ መሆኑን የከተማው ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን አስታወቀ። በባለሥልጣኑ የውሃ አቅርቦትና ሥርጭት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈቃዱ ዘለቀ ለዋልታ እንደገለጹት ፕሮጄክቶቹ አሁን ካለው የውሃ አቅርቦት በተጨማሪ በቀን 249 ሺ ሜትር ኩብ ውሃ ለማቅረብ የሚያስችሉ ናቸው። - ; ፕሮጀክቶቹ ከፊታችን መስከረም ጀምሮ እስከ ግንቦት ወር ድረስ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት የሚጀምሩ ሲሆን ይህም አሁን በከተማው በቀን የሚሠራጨውን 350 ሺ ሜትር ኩብ ውሃ ወደ 599ሺ ሜትር ኩብ እንደሚያሳድገው አስረድተዋል ። እንደ አቶ ፈቃዱ ገለጻ ከፕሮጀክቶቹ መካከል በቀን 70ሺ ሜትር ኩብ ውሃ የማምረት አቅም ያለው የአቃቂ ከርሰ ምድርና ጥልቅ ውሃ ስሪ ‘ኤ’ ተብሎ የሚጠራው ፕሮጀክት በመጪው መስከረም ወር አገልግሎት መሥጠት የሚጀምር ሲሆን ሌላኛውና 70ሺሜትር ኩብ ማምረት የሚችለው የአቃቂ ከርሰ ምድርና ጥልቅ ውሃ ስሪ ‘ቢ’ የተባለው ፕሮጀክት ደግሞ በየካቲት ወር ለአገልግሎት ይበቃል - ; በተጨማሪም የለገዳዲ የከርሰ ምድር ውሃ ላይ የማስፋፊያ ሥራ በማካሄድና የድሬ ግድብን በማሻሻል እንዲሁም የምዕራፍ ሁለት የአቃቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክትን በ2007 ዓም በማጠናቀቅ በአጠቃላይ 88ሺ ሜትር ኩብ ውሃ በአዲስ አበባ ከተማ የማሠራጨት አቅም ይፈጠራል ብለዋል - ; በከተማው የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች 20 ጥልቅ ጉድጓዶችን በመቆፈር በቀን 21ሺ ሜትር ኩብ ውሃ ለማምረት ባለሥልጣኑ ጥረት እያደረገ ነው ያሉት አቶ ፈቃዱ እስካሁን አራት ጉድጓዶች መቆፈራቸውን ገልጸዋል። ከውሃ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ችግሮች ሲያጋጥሙ በህብረተሰቡ ጥቆማ ማስተካከያዎች እንደሚደረጉ የጠቆሙት አቶ ፈቃዱ ለህብረተሰቡ ያለውን ተደራሽነት ይበልጥ ለማሻሻልም ባለስልጣኑ የራሱን የስልክ ጥሪ ማዕከል ለመቋቋም በዝግጅት ላይ  መሆኑን ገልጸዋል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
433
ባለፉት 4 ዓመታት 31 ሚሊዮን ህዝብ የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ሆኗል , - 1.3; .._2014. 0 262 197 ; 5; አዲስ አበባ ፣ መስከረም 28 2007 (ዋኢማ) - በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ አራት ዓመታት ውስጥ በመላው አገሪቱ ከ31 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ መሆኑን የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ። በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ እንደገለጹት  በመጠጥ ውኃ አቅርቦት ጥረቱ ከተማና ገጠርን ጨምሮ አገራዊ የንጹህና ዘላቂ መጠጥ ውኃ ሽፋኑን 76 ነጥብ 7 በመቶ እንዲደርስ እንዳደረገው ገልጸዋል። ከተቀመጠው ግብ ጋር ሲነፃፃርም በገጠር 103 ነጥብ 2 በመቶ በከተማ 123 ነጥብ 1 በመቶ እንዲሁም ከጠቅላላው 105 በመቶ ማሳካት መቻሉን አመልክተዋል። በእቅድ ዘመኑ ውስጥ በ1 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ በነፍስ ወከፍ በቀን 15 ሊትር ውኃና በከተማ በግማሽ ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ በነፍስ ወከፍ በቀን 20 ሊትር ውኃ ለማቅረብ እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም በመላው አገሪቱ ከ10 ሚሊዮን በላይ ህዝብን የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።   ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
434
ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሆኑ , - ; .._2014_22_14. 0 257 193 ; 5; አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 122007 (ዋኢማ) - ባለፉት አራት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ትግበራ ዓመታት ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸውን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ እንደገለጹት የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል 28 ሚሊየን በላይ የሚሆኑት በገጠር የሚኖሩ ሲሆኑ ቀሪዎቹና ከ3 ነጥብ 24 ሚሊየን በላይ የሚሆኑት ደግሞ በከተማ የሚኖሩ ናቸው። ባለፉት አራት ዓመታት ባጠቃላይ 29 ነጥብ 78 ሚሊየን ያህል ዜጎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ የእቅዱን 105% ማሳካት መቻሉን ተናገረዋል።    አቶ ብዙነህ አያይዘው እንደገለጹት ባለፉት አራት ዓመታት በገጠር 76,354 እንዲሁም በከተማ 214 የውሃ ተቋማት ግንባታ፣ የማስፋፊያና የመልሶ ማቋቋም ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ የመሳሪያዎች ፣ የተቋራጮችና ባለሙያዎች እጥረት እንዲሁም በየደረጃው ያሉ የአስፈፃሚ አካላት የክትትል፣ ግምገማና ግብረ መልስ አቅም ውስንነት በዕቅዱ ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ችግሮች መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመኑ ማብቂያ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቱን በገጠር በነፍስ ወከፍ በቀን 15 ሊትር በከተማ ደግሞ 20 ሊትር ለማድረስ የተቀመጠውን ግብ  ለማሳከት ሚኒስቴሩ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
435
የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ሙሉ በሙሉ ይሳካል- የሚኒስቴሩ, - ; .._2015_14. 0 260 172 ; 5; አዲስ አበባ ፣ ጥር 6 2007 (ዋኢማ) - የአገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ሙሉ በሙሉ እንደሚሳካ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ - ; የሚኒስቴሩ የኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ እንደገለፁት በ2006 በጀት ዓመት መጨረሻ ሀገር አቀፉ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት 76.7 በመቶ ደርሷል። - ; አቅርቦቱ በተያዘው የበጀት ዓመት መጨረሻ 80.83 የሚደርስ ሲሆን በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ውስጥ ሽፋኑን ሙሉ በመሉ ለማሳካተ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ - ; የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦቱን ለማሟላት በየአመቱ ከአምስት እስከ ሰባት ቢሊዮን ብር በጀት እየተመደበ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታና ማስፋፊያ እንደሚካሄድ ኃላፊው አስረድተዋል፡፡ - ; እንደ አቶ ብዙነህ ገለጻ በ2003 ዓም በተደረገ ቆጠራ በአገሪቱ ያሉት አጠቃላይ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ብዛት 94ሺህ 400 የነበር ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ቁጥሩ 161ሺህ 813 ደርሷል፡፡ - ; ተጨማሪ የውሃ ተቋማትን ለመገንባት ጥረት እየተደረገ ሲሆን በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል መሳሪያዎች እጥረት እንዲሁም የኮንትራክተሮችና አማካሪዎች አቅም ውስንነት በዘርፉ የተጋረጡ ተግዳሮቶች እንደሆኑ ኃላፊው ተናግረዋል። - ; ተግዳሮቶቹን ለመፍታትም በአገሪቱ ካሉ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችና የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ባለሙያዎችን ለማፍራት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየሰራ መሆኑን አቶ ብዙነህ አስረድተዋል፡፡),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
436
ኢትዮጵያ በንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ አሳካች , - ; .._2015_23. 0 281 210 ; 5; አዲስ አበባ፤ መጋቢት 142007(ዋኢማ)-- ኅብረተሰቡን የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ለማድረግ የተቀመጠውን የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ ማሳካቷ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። በተያዘው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ የሚጠናቀቀው በንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ዘርፍ የምዕተ ዓመቱ የልማት ግብ አቅርቦቱን በግማሽ ማሳደግ እንደሆነ የመንግሥታቱ ድርጅት መረጃ ያመለክታል። ሚኒስትሩ እንደሚሉት አገሪቱ ለንፁህ መጠጥ ውኃና ሳኒቴሽን አገልግሎት ትኩረት በመስጥት የንፁህ መጠጥ ውኃ ተቋማትን ተደራሽ ማድረግ በመቻሏ በመስኩ የተቀመጠውን የምዕ ዓመቱን ግብ አሳክታለች። ሚኒስቴሩ 22ኛው ዓለም አቀፍ የውኃ ቀንን ውኃና ዘላቂ ልማት በሚል መሪ ቃል ትናንት በተለያዩ ዝግጅቶች ያከበረ ሲሆን በዘርፉ የልማት ሥራዎች በመስራት ሞዴል ለሆኑ ወረዳዎችና ተቋማት እውቅና ሰጥቷል። ተሸላሚዎቹ ከ9 ክልሎችና ከሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች በራስ አገዝ የመጠጥ ውኃ መርሃ ግብር፣ በውኃ፣ በመስኖ እና በኢነርጂ ዘርፍ አፈፃጸም ውጤታማ የሆኑ ናቸው። ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ እንደገለጹት በገጠር ያለው የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት 75 ነጥብ 5 በመቶ የደረሰ ሲሆን በከተማ ደግሞ 84 ነጥብ 2 በመቶ ማድረስ ተችሏል ። በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱም የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት 29 ነጥብ 8 ሚሊዮን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ በአራት ዓመት ውስጥ 31 ነጥብ 3 ሚሊዮን ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል ። ከ1984 ዓ.ም ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ከፍተኛ ትኩረት በ2006 በጀት ዓመት መጨረሻ የአገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ወደ 76 ነጥብ 7 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ አስታውቀዋል ። ለዚህ ስኬትም የአገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦች ሕዝቦች፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተዋጽኦ ተጠቃሽ መሆኑን አስረድተዋል ። ከ23 ዓመታት በፊት የአገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት 19 ነጥብ 2 በመቶ እንደነበር ከሚኒስቴሩ የተገኘ መረጃ ያሳያል። (ኢዜአ) );
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
437
በአገሪቱ የንጹህ ውሃ መጠጥ ሽፋን 79 በመቶ መድረሱን ሚኒስቴሩ አስታወቀ ። , - ; .._2015 24. 0 ; 5; አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 162007(ዋኢማ)-የአገሪቱ አጠቃላይ የንጹህ ውሃ መጠጥ ሽፋን 79 በመቶ  መድረሱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር  አስታወቀ ። - ; የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ከበደ ገርባ ለዋልታ እንደገለጹት በአገሪቱ የገጠርና ከተማ አካባቢዎች የንጹህ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መሠረት በተካሄደው እንቅስቃሴ የአገሪቱ አጠቃላይ የንጹህ ውሃ ሽፋን 79 በመቶ ደርሷል ብለዋል። - ; ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የአገሪቱን የንጹህ ውሃ ፍላጎት ለሟሟላት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አስፈላጊውን በጀት በመመደብ ሥራዎችን እያካሄደ ነው ያሉት አቶ ከበደ  በአሁኑ  ወቅት  የከተማ የንጹህ ውሃ መጠጥ ሽፋን 86 በመቶ የገጠር የንጹህ መጠጥ ሽፋን 78 በመቶ መሆኑን  ገልጸዋል። - ; ባለፉት አራት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዓመታት ሚኒስቴር መሥሪያቤቱ 32ነጥብ5 ሚሊዮን  ሚሊዮን  ህዝብ  የንጹህ ውሃ ተጠቃሚ  ለማድረግ ዕቅድ ተይዞ የአገሪቱ የንጹህ ውሃ ሽፋን በየዓመቱ 8 በመቶ ዕድገትበማሳየት ከ33 ሚሊዮን በላይ ህዝብን ተጠቃሚ በማድረግ  በሚሊኒየም የልማት ግብ በመጠጥ ውሃና ንጽህና የተቀመጠውን ግብ ማሳካት መቻሉን አስረድተዋል ። - ; በዘንድሮ የበጀት ዓመት ሚኒስቴሩ በመላው አገሪቱ 49ሺ አዳዲስ የመጠጥ ውሃ ተቋማትን በመገንባት 15ሚሊዮን ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርግ ዕቅድን ማውጣቱን የገለጹት አቶ ከበደ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 9ሺ የሚሆኑት የመጠጥ ውሃ ተቋማት አገልግሎት ጀምረው 3ነጥብ 6  ሚሊዮን ህዝብን የንጹህ ውሃ  ተጠቃሚ አድርገዋል ብለዋል ። - ; በኢትዮጵያ 80 በመቶ የሚሆነው የመጠጥ ውሃ  ከከርሰ ምድር  እንደሚገኝና  በገጠር የአንድ ሰው  የቀን አማካኝ  የውሃ ፍጆታ 15ሊተር ሲሆን በከተማ 20 ሊትር  መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል ።   ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
438
ንፁሕ የመጠጥ ውሃን ለማዳረስ ይዞት የነበረውን እቅድ ማሳካቱን ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ገለጸ, - ; .._2015_4. 0 261 196 ; 5; አዲስ አበባ፣ ግንቦት 272007 (ዋኢማ) - በንፁሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት በአምስት ዓመቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድም ሆነ በምዕተ ዓመቱ ግቦች ተይዞ የነበረ እቅድ ማሳካቱን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ - ; ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ከበደ ገርባ በተለይ ለዋኢማ እንደገለጹት የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን በከተማ ሙሉ በሙሉ በገጠር ደግሞ 98 በመቶ ለማዳረስ  በአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ የተያዘውን ግብ  ማሳካት ተችሏል ብለዋል፡፡ - ; ለ33 ሚሊዮን ዜጎች የንፁሕ መጠጥ ውሃ ለማዳረስ ታቅዶ እንደነበር የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው በአሁኑ ወቅት 34.8 ሚሊዮን ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ብለዋል። - ; በዓለም ዓቀፍ ደረጃም የምዕተ አመቱን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት በፊት ከነበረበት 14 በመቶ ወደ 60 በመቶ ለማድረስ ግብ ተጥሎ እንደነበር አስታውሰው ሽፋኑን 80 በመቶ ማድረስ በመቻሉ የምዕተ አመቱን ግብ ቀድሞ ማሳካት እንደተቻለ ጠቁመዋል፡፡ - ; ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በያዝነው የበጀት ዓመት መጨረሻ ላይ አቅርቦቱን ወደ 86 በመቶ ለማድረስ እየሰራ እንደሆነም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል። - ; በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ በውሃ ማከፋፈያ ተቋማት ግንባታ 89 ሺህ አዳዲስ የውሃ ተቋማትን ለመገንባት ታቅዶ 75 ሺህ እንደደረሰ የገለጹት  አቶ ከበደ  በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድም  170 ሺህ ለመገንባት  ታቅዷል ብለዋል፡፡ - ; በቀጣይ የእድገትና ትራንስፎርማሽን እቅድ በከተማ እስከ 500 ሜትር ርቀት ያለውን  የንፁህ መጠጥ አቅርቦት ወደ አባወራ፣ በገጠር ደግሞ ከ1.5 ኪሎሜትር ርቀት ወደ 1 ኪሎሜትር ለማሳጠር ታቅዷል ብለዋል። - ; በአምስቱ ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን የዕቅድ ጊዜ ለንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ግንባታ ከ30 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
439
 በአዳማ ከተማ ላለፉት ቀናት የተቋረጠው የንፁህ መጠጥ ውሀ ችግር እስከ ነገ ምሽት ይፈታል ተባለ, በአዳማ ከተማ ላለፉት ጥቂት ቀናት የተቋረጠው የንፁህ መጠጥ ውሀ ችግር እስከ ነገ ምሽት ድረስ የክልሉ የውሀና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ። በአዳማ ከተማ  የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት ከተቋረጠ አስራ ስምንት ቀናት ሆኖታል። የከተማ አስተዳደሩና የውሀና ፍሳሽ ፅህፈት ቤት ችግሩ የተከሰተው ከቆቃ ወደ አዳማ የሚመጣው የውሀ መስመር ላይ በደረሰ አደጋ ነው ብሏል። ከዚህ በፊት የውሀ መቆራረጥ ሲያጋጥም አስተዳደሩ በፍጥነት ችግሮቹን ለመፍታት ጥረቶችን ሲያደርግ የቆየ ቢሆንም ፥ የአሁኑ ችግር ከበድ ያለ መሆኑ ለቀናት እንዲቆይ እንዳደረገው ነው ሀላፊዎቹ የተናገሩት። ችግሩን ለመፍታትም ርብርብ እየተደረገ መሆኑንና ፥ በአሁኑ ጊዜም በቦቲና በሌሎች መንገዶች ለነዋሪው ውሀ እየቀረበ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። የከተማው ነዋሪ ችግሩን ለመፍታት እየተደረገ ያለውን ጥረት በማየት እያሳየ ላለው እገዛና ትእግስት ምስጋናችንን እናቀርባለንም ማለታቸውን ፋና ዘግቧል። ከችግሩ ስፋትና መልሶ ለመጠገን የሚደረገውን ጥረት ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ተደጋጋሞ በሚደርስ የጎርፍ አደጋ ሌላው ስራውን በፍጥነት እንዳይጠናቀቅ አድርጎታል። በአሁኑ ጊዜ ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝና ከ48 ሰአት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ መፍትሄ እንደሚያገኝ ያላቸውን ተስፋ የገለጹት ደግሞ በውሀና ኢነርጂ ሚንስቴር የውሃ ሳኒቴሽን ዳይሬክተር አቶ ዮሀንስ ገብረመድህን መግለጻቸውን ፋና ዘግቧል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
440
 የሀገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ቁጥር 90 ሺ መድረሱ ተገለፀ, የሀገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ቁጥር ከ90 ሺ በላይ ማድረስ መቻሉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ገለጹ። ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ከበደ ገርባ ዛሬ በድሬዳዋ ከተማ በሀገሪቱ የውሃ አጠቃቀም ሁኔታ ላይ ያተኮረ 6ኛ ሀገር አቀፍ የውሃ አገልግሎቶች ስብሰባ ላይ እንደተናገሩት፤ ቁጥሩ ሊጨምር የቻለው መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ነው። አቶ ከበደ  አያይዘው እንደገለጹት የሀገሪቱን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ቁጥርን በማሳደግ ጤናማና አምራች ህብረተሰብ የመፍጠር ራዕይ ፍሬ ማሳየት ጀምሯል።   ሀገሪቱን ኢህአዴግ ማስተዳደር ከጀመረበት ወቅት ጀምሮ ትክክለኛ የውሃ ሀብት ልማት ፖሊስና ስትራቴጂ በመንደፍና ህብረተሰቡን በስፋት በማሳተፍ ለመጠጥና ለግብርና ኢንዱስትሪና ለኃይል ማመንጫ አገልግሎቶች ለማዋል ከፍተኛ ርብርብ ተደርጓል ብለዋል።    ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ከበደ አክለውም ግብርናችንን ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ ህብረተሰቡ በሰራዊት መልስ ተደራጅቶ የተፈጥሮ ሀብታችንን እየተንተካከበ ነው። በተለያዩ ዘዴዎችም ውሃን ይዞ በማቆየት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሄክታር መሬትን በመስኖ በማልማት በዓመት ሁለትና ከዚያ በላይ ማምረት ተችሏል። በማለት ገልፀዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አሰድ ዜያድ በበኩላቸው፤ በአስተዳደሩ ከፍተኛ የውሃ ክምችት ቢኖርም በየጊዜው እየጨመረ ከሚመጣው የህዝብ ቁጥርና ኢንቨስትመንት ከማስተናገድ አኳያ የማስፋፋት ስራዎች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል። ችግሩን ለመቅረፍም ከመንግስትና ከዓለም ባንክ በተገኘ ከ570 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ የማስፋፋት ስራዎችን ለመስራት ስምምንት ላይ መደረሱን አያይዘው ገልፀዋል። ለሶስት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ስብሰባ ላይ ከ450 በላይ ሰዎች ተሳታፊዎች ሲሆኑ፤ በስብሰባው ላይም ውኃ ተኮር ጥናታዊ ጽሁፎች እንደሚቀርቡ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
441
ባለስልጣኑ የከተማዋን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ለማሻሻል እየሰራ ነው, የአዲስ አበባ ከተማን የውኃ አቅርቦት ለማሻሻል ሶስት ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ፕሮጀክቶች ሊያካሂድ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ።    የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ደጋፊ የስራ ሂደት መሪ ወይዘሮ እፀገነት ተስፋዬ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ ሶስቱ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በቀን ከ150 ሺ ሜትር ኪዩብ በላይ ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ይሰጣሉ። ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ የሚያስፈልገውን ወጪ ከኢትዮጵያ መንግስት፣ ከዓለም ባንክና ከቻይናው ኤግዚም ባንክ በረዥም ጊዜ የሚከፈል ብድር የተገኘ ሲሆን፤ ፕሮጀክቶቹ በ2006 ዓመተ ምህረት ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። እንደ ወይዘሮ እፀገነት ገለፃ ከሚሰሩት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከዓለም ባንክ በተገኘ 830 ሚሊዮን ብር የሚከናነወን ሲሆን፤ 70ሺ ሜትር ኪዩብ ውሃ ማመንጨት አቅም ይኖረዋል ብለዋል። እንዲሁም ሌላው 70ሺ ሜትር ኩዩብ ንፅህ የመጠጥ ውሃ ሊያቀርብ የሚችለው ፕሮጀክት ከቻይና ኤግዚም ባንክ በረዥም ጊዜ በሚከፈል 94 ሚሊዮን ዶላር ብድር የሚከናወን መሆኑንም ጠቁመዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁም በተለይም ለቡ፣ ዓለም ባንክ፣ ጦር ኃይሎች፣ ቤተልና ሌሎች አካባቢዎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋን የተሻለ እንደሚያደርገው ተናግረዋል። እንዲሁም በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የውሃ አቅርቦት ውስንነት በሚታይባቸው የከተማዋ አካባቢዎችም 10ሺ 700 ሜትር ኪዩብ ውሃ በቀን መስጠት የሚችሉ ስምንት የውሃ ጉድጓዶች ቁፋሮ በማካሄድ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ ለፕሮጀክቱ ማስኬጃም 100 ሚሊየን ብር በጀት መመደቡን ገልፀዋል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
442
 ሚኒስቴሩ ከ413 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ እያካሄደ ነው , የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ለማሻሻል በዘንድሮው የበጀት ዓመት ከ413 ሚሊየን ብር በላይ የተለያዩ የውሃ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ዛሬ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ ሚኒስቴሩ በዘንድሮው የበጀት ዓመት 413 ሚሊየን 798 ሺ ብር ወጪ በማድረግ 7 ሚሊየን የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ነው። በዚህም በገጠር 6 ሚሊዮንና በከተማ ደግሞ 1 ሚሊዮን የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከክልሎችና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በጋራ እየሰራ ነው ብለዋል። በሰባት ዞኖች 12 የፍሎራይድ ማጣሪያ ገንዳዎች ግንባታ የሚካሄድ መሆኑን አቶ ብዙነህ ተናግረዋል። ለግንባታው የሚሆነውን ወጪ ከዓለም ባንክ፣ አፍሪካ ልማት ባንክ፣ ከዩኒሴፍ፣ ከፊንላንድ መንግስት፣ ከጣሊያንና ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር፣ ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲና አገር በቀል ከሆኑ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶችና ከክልሎች የተገኘ ነው ብለዋል። በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አመቱ መጨረሻ አሁን ያለውን 79 ነጥብ 8 በመቶ አማካኝ ሀገራዊ የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ወደ 87 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አቶበ ዙነህ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
443
ከ12 ሚሊየን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሆኑ, - ; .._2013. 0 260 195 ; 5; አዲስ አበባ፤ የካቲት 272005ዋኢማ - የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ12 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻሉን አስታወቀ። በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለ11 ነጥብ 1 ሚሊየን የገጠርና 1 ነጥብ 1 ሚሊየን የከተማ ነዋሪዎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ አድርጓል። ተጠቃሚ ያደረገው ባለፉት ሁለት ዓመት ከስድስት ወራት ማለትም በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አመቱ ግማሽ ላይ በድምሩ 24ሺ 320 የገጠርና የከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት በመገንባት ነው። አገልግሎት የማይሰጡ የመጠጥ ውሃ ተቋማት ቁጥርን ከመቀነስ አንፃርም ከ8ሺ 896 በላይ ነባር የገጠር መጠጥ ውሃ ተቋማት ተጠግነው አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገዋል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ በ84 ከተሞች አዲስ የመጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ የማስፋፊያና የመልሶ ማቋቋም ሥራዎች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በአምስት አመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ 18 ነጥብ 2 ሚሊየን የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ እቅድ በመያዝ ወደ ትግበራ ከገባ ሁለት አመት ከስድስት ወር አስቆጥሯል። የተቀመጠውን አጠቃላይ ግብ ለማሳካትም 26ሺ 739 የእጅ ጉድጓድ፣ 7ሺ 372 መለስተኛ ጥልቅ ጉድጓዶችና 7ሺ 212 የምንጭ ማጐልበት ሥራዎች ለማከናወን ታቅዷል። እንዲሁም 335 የውሃ ማጠራቀሚያ ኩሬዎች፣ 545 የዝናብ ውሃና 23 የገፀ-ምድር የመጠጥ ውሃ መጠራቀሚያ ጋኖችን በመገንባት ህብረተሰቡን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን አቶ ብዙነህ ቶልቻ ተናግረዋል። በአጠቃላይ በእድገትና በትራንስፎርሜሽን እቅዱ የገጠር የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋንን በ1 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ በነፍስ ወከፍ በቀን 15 ሊትር እንዲያገኙ አስችሏቸዋል። እንዲሁም በከተማ ያለውን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን በ0 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ በነፍስ ወከፍ በቀን 20 ሊትር እንዲያገኙ በማድረግ በአገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን 98 ነጥብ 5 በመቶ የማድረስ አጠቃላይ ግብ ተጥሎ ወደ ስራ መገባቱ የሚታወስ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
444
የከተማዋን የመጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ በ580 ሚሊየን ብር የማስፋፊያ ስራ እየተካሄደ ነው, - ; .._2013. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ፤ መጋቢት 52005ዋኢማ - የከተማዋን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ በ580 ሚሊየን ብር የለገዳዲ የውሃ ማጣሪያ ጣቢያና የድሬ ግድብ ማስፋፊያን እያከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ። በባለስልጣኑ የፕሮጀክት ልማትና ማስፋፊያ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ስዩም ብርሃኑ እንደገለፁት፤ የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ የድሬ ግድብ ውሃ የመያዝ አቅምን በማሳደግ የለገዳዲ ግድብ 30ሺ ሜትር ኪዩብ ተጨማሪ ጥሬ ውሃ ማቅረብ የሚችልበትን አቅም ይፈጥራል። ፕሮጀክቱ የለገዳዲ የውሃ ማጣሪያ ጣቢያ የማምረት አቅምን በ30ሺ ሜትር ኪዩብ የሚያሳድገው ሲሆን፤ ግድቡ በቀን የሚያመርተውን 165ሺ ሜትር ኪዩብ ውሃ ወደ 195ሺ ያሳድገዋል ብለዋል። ይህም በከተማዋ ሰሜናዊና ሰሜን ምስራቅ አካባቢ ያለውን የውሃ አቅርቦት እንደሚያሻሽለው  ኢንጂነር ስዩም ተናግረዋል። ለፕሮጀክቶቹ ማስፈፀሚያ 580 ሚሊየን ብር በጀተ የተመደበ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ለድሬ ግድብ ማስፋፊያ 130 ሚሊየን ብር፣ 430 ሚሊየን ብሩ ደግሞ ለለገዳዲ የውሃ ማጣቢያ ግንባታና ቀሪው ብር በሀገሪቱ የመጀመሪያ የሆነ የክሎሪን ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ የሚውል መሆኑ ተጠቁሟል። በአሁኑ ወቅት የድሬ ግድብ ማስፋፊያ ስራ በ16 ወራት ለማጠናቀቅ የታቀደ ሲሆን፤ የጠቅላላ ስራው 15 በመቶ መጠናቀቁም ተጠቁሟል። የለገዳዲ ማጣሪያ ጣቢያ የማስፋፊያና የክሎሪን ፋብሪካ ግንባታ ስራው ደግሞ በ24 ወራት ጊዜውስጥ ሊጠናቀቅ እንደሚችል ኢንጂነር ስይም መግለፃቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
445
የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን 61 ነጥብ 6 በመቶ መድርሱ ተገለፀ, - ; .._2013_. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 32005 (ዋኢማ) - በመላው ሀገሪቱ በተካሄደ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሳኒቴሽንና ሃይጂን ተቋማት ቆጠራ አገራዊ የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን 61 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። የሚኒስቴሩ የውጭና የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ሳኒቴሽንና ሃይጂን ተቋማት ቆጠራ መሰረት እስከ 2005 ዓ.ም አጋማሽ ድረስ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት በገጠር 58 ነጥብ 71 በመቶ በከተማ ደግሞ 80 ነጥብ 72 በመቶ ደርሷል። ይህም አጠቃላይ አገራዊውን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት 61 ነጥብ 6 በመቶ ያሳደገው ሲሆን፤ በ2007 ዓ.ም ማለትም የሚሊኒየም የምዕት አመቱ የልማት ግብ ሀገራዊውን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት 70 በመቶ ለማድረስ የታቀደውን ዕቅድ ማሳካት እንደሚቻል በቆጠራው የተገኘው ውጤት አመላካች ነው ብለዋል። ቆጠራው በ2003 ዓ.ም መካሄዱን የገለፁት አቶ ብዙነህ፤ በቆጠራው ወቅትም በ12 ሚሊየን አባወራዎች የቤት ለቤት ቆጠራ ተካሂዷል ብለዋል። የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ ሳኒቴሽንና ሃይጂን አገልግሎት ክትትልና ግምገማ ማካሄድ ክፍተት አመልካች መሆኑ ስለታመነበት በ2003 ዓ.ም. ጀምሮ በአለም አቀፍ ደረጃ ሲምፖዚየም መካሄድ መጀመሩን ጠቁመው፤ ከመጋቢት 30 ጀምሮ እስከ ዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል ሲምፖዚየሙ በመካሄድ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። ሲምፖዚየሙን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ከአይአርሲ አለም አቀፍ የውሃና ሳኒቴሽን ማዕከል ጋር በጋራ በመሆን እየተካሄደ ሲሆን፤ በውይይቱ የመጀመሪያው የተቋማት ቆጠራ ግኝት፣ የተቋማቱ ቆጠራ በዳታ መሰባሰብና መተንተን፣ ሪፖርት አደራረግና ወደፊት ዳታን ወቅታዊ የማድረግ እቅድና መረጃን ለመረጃ ፈላጊዎች ተደራሽ ማድረግ ላይ የልምድ ልውውጥ እንደሚደረግም አቶ ብዙነህ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
446
“ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት ከ12 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሆኗል” አቶ አለማዮሁ ተገኑ, .._2013. 0 260 195 ; 5; አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 42005 (ዋኢማ) - ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት 12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ህዝብ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረጉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስትሩ አቶ አለማዮሁ ተገኑ በተለይ ለዋልታ እንደገለጹት በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ 16 ሚሊዮን ህዝብ  ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እንደነበር አስታውሰው ቀሪው 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ህዝብ በቀጣይ ተጠቃሚ  ይሆናል ብለዋል። በአገሪቱ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ለማዳረስ የህዝብና የአመራር ንቅናቄ በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ እስካሁን ባለው ጊዜ ሽፋኑ 61 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን  አስታውቀዋል። ሚኒስትሩ አያይዘውም  በገጠር 93 ሺሕ  በከተማ  ደግሞ 1 ሺሕ 5 መቶ የውሃ ተቋማት ቆጠራና የሚገኙበትን ደረጃ የመለየት ስራ እንደተከናወነ ተናግረዋል።   አቶ አለማዮሁ አያይዘውም የአገሪቱ የመስኖ ስራ የሚከናወነው በፌዴራል መንግስት፣ በክልሎች፣ በመንግስት የልማት ድርጅቶችና  በግል ባለሃብቶች እንደሆነ ጠቁመው በጥናትና በቅድመ ዝግጅት ደረጃ በሁሉም ወገኖች መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመስኖ ስራ ሰፊና ከባድ አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ አገሪቱ ካላት  የመስኖ ሃብት አንጻር  ብዙ እንደሚቀር አቶ አለማዮሁ ተናግረዋል። አገሪቱ ካላት 1 መቶ 22 ቢሊየን ሜትር ክዩቢክ ውሃ እስካሁን ድረስ የተጠቀመችው  7 በመቶ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመን የመስኖ ስራ ከነበረበት 2 ነጥብ 5 ወደ 15 በመቶ ለማሳደግ እቅድ ተይዞ  7 በመቶ መፈጸሙን የጠቆሙት  ሚኒስትሩ  በቀሪው ጊዜ እቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
447
በቤንሻንጉል ጉምዝ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ለማሳደግ የከርስ ምድር ጥናት እንዲካሄድ ተጠየቀ ። በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማሳደግ የኮርስ ምድር ውሃ ጥናት መካሄድ እንዳለበት ተጠቆመ ፤ በክልሉ በገጠር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችል መመሪያም ተዘጋጅቷል ። የክልሉ ውሃ ማእድንና እነርጂ ቢሮ የክልሉ የገጠር መጠጥ ውሃ አስተዳደር ለማሻሻል ላለፉት ሶስት ቀናት ባካሄደው አውደ ጥናት ማጠናቀቂያ ላይ እንደተገለጸው በክልሉ እስካሁን የከርሰ ምድር ውሃ ትናት ባለመካሄዱ በውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታና አስተዳደር ላይ ችግር ሲፈጠር ቆይቷል ። በቀጣይ ግን በክልሉ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እገዛ በመጠየቅ ትናቱን ለማካሄድ ትረት እንደሚደረግ ቢሮው አስታውቋል ። የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች እንዳሉት ያለ በቂ ትናት የተቆፈሩ የመለስተኛ የእጅና ትልቅ ጉድጓዶች ባልተጠበቀ ወቅት ምንጫቸው ደርቆ አቅርበታቸው ስለሚቋረጥ ሀብረተሰቡ ተገቢ አገልግሎት በማግኘት ላይ አይደለም ። በመሆኑም ቢሮው የከርሰ ምድር ውሃ ትናት በማካሄድ በቂ የውሃ ክምችት ያለባቸውና ቁፋሮ የሚካሄድባቸው ቦታዎች የሚለዩበትና የተገነቡ ፕሮጀክቶች አስተዳደራዊ ችግሮች የሚወገዱበት መንገድ ማመቻቸት እንዳለበት ተቁመዋል ። በሌላ በኩል በክልሉ በገጠር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ የተሳተፉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ወጥነት ባለው አሰራር እንዲመሩና ተግባራቸውንም መቆጣጠር የሚያስችል የአፈጻጸም መመሪያ ማዘጋጀቱን ቢሮው አስታውቋል ። የተዘጋጀው መመሪያ ድርጅቶቹ በመስኩ የሚያካሄዱትን እንቅስቃሴ በተቀናጀ መንገድ ለማጎልበትና በአንጻሩም ከክልሉ ውሃ ማእድንና እነርጂ ሃብት ቢሮ አሰራር ውጪ የሚንቀሳቀሱትንና ታማኝነት የጎደላቸውን ድርጅቶች በመለየት እርምጃ ለመውሰድ እንደሚያግዝ በአውደ ጥናቱ መገለጹን ዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል ዘግቧል ። በአሁኑ ወቅትም የክልሉ የንጹህ የመጠጥ ውሃ ሽፋን 27 በመቶ ብቻ እንደሆነ ከቢሮው የተገኘ መረጃ ያመለክታል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
448
 “ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት ከ12 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሆኗል” አቶ አለማዮሁ ተገኑ, ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት 12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ህዝብ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረጉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስትሩ አቶ አለማዮሁ ተገኑ በተለይ ለዋልታ እንደገለጹት በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ 16 ሚሊዮን ህዝብ  ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እንደነበር አስታውሰው ቀሪው 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ህዝብ በቀጣይ ተጠቃሚ  ይሆናል ብለዋል። በአገሪቱ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ለማዳረስ የህዝብና የአመራር ንቅናቄ በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ እስካሁን ባለው ጊዜ ሽፋኑ 61 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን  አስታውቀዋል። ሚኒስትሩ አያይዘውም  በገጠር 93 ሺሕ  በከተማ  ደግሞ 1 ሺሕ 5 መቶ የውሃ ተቋማት ቆጠራና የሚገኙበትን ደረጃ የመለየት ስራ እንደተከናወነ ተናግረዋል።   አቶ አለማዮሁ አያይዘውም የአገሪቱ የመስኖ ስራ የሚከናወነው በፌዴራል መንግስት፣ በክልሎች፣ በመንግስት የልማት ድርጅቶችና  በግል ባለሃብቶች እንደሆነ ጠቁመው በጥናትና በቅድመ ዝግጅት ደረጃ በሁሉም ወገኖች መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመስኖ ስራ ሰፊና ከባድ አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ አገሪቱ ካላት  የመስኖ ሃብት አንጻር  ብዙ እንደሚቀር አቶ አለማዮሁ ተናግረዋል። አገሪቱ ካላት 1 መቶ 22 ቢሊየን ሜትር ክዩቢክ ውሃ እስካሁን ድረስ የተጠቀመችው  7 በመቶ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመን የመስኖ ስራ ከነበረበት 2 ነጥብ 5 ወደ 15 በመቶ ለማሳደግ እቅድ ተይዞ  7 በመቶ መፈጸሙን የጠቆሙት  ሚኒስትሩ  በቀሪው ጊዜ እቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
449
 የጎንደር ከተማ ዘላቂ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ዛሬ ተመረቀ 166 ሺ ህዝብ የውሃ ተጠቃሚ ሆነ ። ለአራት አመታት በ74 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ሲካሄድ የቆየው የጎንደር ከተማ ዘላቂ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ። ፕሮጀክቱን መርቀው የከፈቱት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ ዮሴፍ ረታ እንደተናገሩት ከጅምር እስከ ፍጻሜ የከተማው ነዋሪዎች ከመንግስት ጎን ቆመው ያደረጉት ተሳትፎ የሚያበረታታ ነው ፤ የክልሉ ውሃ ማእድንና እነርጂ ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ አበበ አየነው በበኩላቸው በክልሉ መንግስት በጀት የተገነባው ፕሮጀክት ለ20 አመታት ያለምንም ችግር ለ166 ሺ ህዝብ አገልግሎት መስጠት እንደሚችል አስታውቀዋል ። ከአንገረብ ግድም የተጠለፈው የጎንደር ከተማ የውሃ ፕሮጀክት በከተማው የነበሩ 14 ትልቅ የውሃ ጉድጓዶች አማካኝነት 1ሺ 700 ሜትር ኪዩብ ውሃ በማምረት ለከተማው ህዝብ እንደሚያሰራጭ ሃላፊው ተቁመዋል ። በክልሉ ባህርዳር ፣ ደሴና ደብረብርሃን በመሳሰሉ ከተሞች የክልሉ መንግስት በመደበው በጀትና በእርዳታ የውሃ ፕሮጀክቶች እየተካሄዱ መሆኑን ሃላፊው ቸምረው ገልጸዋል ። የነዋሪዎቹ ተወካይ አምባሳደር ዘመረ ካሴ በበኩላቸው ለበርካታ አመታት የነበረው የመጠጥ ውሃ ችግር በመቃለሉ የነዋሪዎችን የቀጣይ የእድገት አቅጣጫ የሚያመላክት ነው ብለዋል ። በቀጣይም ተገቢ በሆኑ የልማት ዘርፎች ላይ እንደሚሳተፉና ለፕሮጀክቱም አስፈላጊ እንክብካቤ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል ። በእለቱ የውሃ ሀብት ልማት ሚኒስቴር አቶ ሽፈራው ጃርሶን ቸምሮ ሌሎች ትሪ የተደረገላች እንግዶችና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የከተማው ነዋሪዎች መገኘታቸውን ዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል ዘግቧል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
450
ማረት ያስገነባቸው 146 የውሃ ፕሮጀክቶች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ ። ማሀበረ ረዴት ትግራይ /ማረት/ በ3 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር ያስገነባቸው 146 የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ ። በድርጅቱ የመጠጥ ውሃ አገልግሎት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ሃይሌ እንደገለጹት በማእከላዊ ፣ ደቡባዊና ምስራቃዊ ዞኖች ባለፉት ስድስት ወራት ያስገነባቸው 25 መካከለኛ ፣ 103 የእጅ ፓምፕ ጉድጓዶች ቁፋሮና 18 የጎለበቱ ምንጮች ከ544 ሺ በላይ ነዋሪዎች ተጠቃሚ አድርገዋል ። በግንባታው የአካባቢው ነዋሪዎች 390ሺ ብር የሚገመት የድንጋይ ፣ አሸዋና ነጻ የጉልበት እገዛ ማድረጋቸውን ገልጸዋል ። በወረራው ወቅት በኢሮብና ጉሎመኸዳ ወረዳዎች የሻእቢያ ወታደሮች ያወደሟቸው 15 የውሃ ፕሮጀክቶች መልሶ በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ መደረጉን ሃላፊው ጠቁመው፤ ቀጣይ ለሚያስገነባቸው 20 የውሃ ፕሮጀክቶች የከርሰ ምድር ትናትና ዲዛይን ስራ መጠናቀቁን አስታውቀዋል ። የክልሉ ውሃ ማእድንና እነርጂ ቢሮ በማካሄድ ላይ ያለውን እንቅስቃሴ ለማገዝም ማረት 85 ሺ ብር የሚያወጡ የውሃ መሳቢያ ሞተሮችና መለዋወጫ መሳሪያዎች በእርዳታ መስጠቱንና በቅርቡም ተመሳሳይ እገዛ ለማድረግ በዝግጅት ላይ እንደሆነ መናገራቸውን ዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል ዘግቧል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
451
 በአማራ 15 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተጠናቅቀው አገልገሎት መስጠት ጀመሩ ። በኢትዮጵያ ማሀበራዊ ተሃድሶ ልማት ፈንድ የአማራ ክልል ጽህፈት ቤት ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ዘንድሮ ካስጀመራቸው 40 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ውስጥ 15ቱ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ጽህፈት ቤቱ አስታወቀ ። በጽህፈት ቤቱ የገጠር መጠጥ ውሃ ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ በቃሉ ትናንት እንደገለጹት በሰሜን ወሎ ፣ ምእራብ ጎጃም ፣ ኦሮሚያና ዋግምራ ዞኖች በሚገኙ ገጠር ቀበሌዎች የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተጠናቅቀው ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ለ21 ሺ ነዋሪዎች አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ። በዞኖቹ አገልግሎት መስጠት ከጀመሩ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መካከል 10 የጎለበቱ ምንጮች ፣ 2 መለስተኛ ትልቅ ጉድጓዶችና አንድ የእጅ ጉድጓድ እንደሚገኙበት ቡድን መሪው ተናግረዋል ። በደጀን ፣ አዋበል ፣ አርጡማጅሌ ፣ ምንጃርሸንኮራ ፣ መርሀቤቴ ፣ ጌራቀያ ፣ አንጎለለና አሳግርት እና መቅደላ ከተሞች በመካሄድ ላይ ያሉ ቀሪዎቹ 25 ፕሮጀክቶች 93 በመቶ የተጠናቀቁ ሲሆን በመጪው ሚያዝያ ለአገልግሎት እንደሚበቁ ቡድን መሪው ማስታወቃቸውን ዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል ዘግቧል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
452
ልማት ፈንዱ ከ18 ሺ የሚበልጡ ነዋሪዎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ አደረገ ። በምስራቅ ሀረርጌ ዞን የኢትዮጵያ ማህበራዊ ተሃድሶና ልማት ፈንድ በመደበው 5 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር ከተጀመሩ 10 የውሃ ፕሮጀክቶች የአራቱ ግንባታ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን የዞኑ ውሃ ፣ ማእድንና ኢነርጂ ልማት መምሪያ አስታወቀ ። የመምሪያው ተወካይ አቶ በርኬሳ ቅጤሳ ዛሬ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማእከል እንደገለጹት ባለፈው አመት በበደኖ ፣ ፈዲስ እና ጐላኦዳ ወረዳዎች ተጀምረው ሰሞኑን አገልግሎት መስጠት የጀመሩ የውሃ ፕሮጀክቶች 18 ሺ 325 ነዋሪዎችን ንጹህ ውሃ ተጠቃሚ አድርገዋል ። ቀሪዎቹ በጐሮጉቱ ፣ ጐላኦዳ እና ፈዲስ ወረዳዎች በመገንባት ላይ ያሉት ስድስት የውሃ ፕሮጀክቶች ከ53 እስከ 93 በመቶ የግንባታ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል ። የውሃ ፕሮጀክቶች እስከ ተያዘው ወር መጨረሻ ይጠናቀቃሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ በርኬሳ ገልጸው ፤ ሲጠናቀቁ 21ሺ 168 ነዋሪዎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
453
የመዲናዋን የውኃ አቅርቦት ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማሳደግ እየተሰራ ነው , - ; .._2015_9. 0 254 199 ; 5; አዲስ አበባ፣  የካቲት 302007(ዋኢማ)- የአዲስ አበባን የንጹህ መጠው ውኃ አቅርቦት ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማሳደግ በውኃ ልማት ዘርፍ መንግሥት ሰፊ ሥራ እየሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ። - ; በቀን 70 ሺህ ሜትር ኪዮብ የማመንጨት አቅም ያለውና ከ 700 ሺህ በላይ የመዲናዋ ነዋሪዎችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ የሚያርገው የአቃቂ ከርሰ ምድር የውኃ ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። - ; የአቃቂ ከርሰ ምድር የውኃ ፕሮጀክት በ2 ቢሊዮን ብር ወጪ ነው ግንባታው የተከናወነው። - ; ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት ባለፉት ጥቂት ዓመታት የከተማውንም ሆነ የአገሪቷን ገጠራማ ክፍል የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ሽፋን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ሲሰራ ቆይቷል። - ; የከተማውን ህዝብ የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ሽፋን ለማሳደግ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ተመድቦ የውኃ ልማት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። - ; ዛሬ በይፋ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የአቃቂ የከርሰ ምድር የውኃ ፕሮጀክትም መንግሥት እየተገበራቸው ከሚገኙ የመስኩ ልማቶች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል። - ; ይህም መንግሥት የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦትን ለማሳደግ የወሰደውን ከፍተኛ ኃላፊነት መገንዘብ ያስችላል ብለዋል። በዚህም የገፈርሳን የውኃ ግድብ የማጠናከሪያ ፕሮጀክት በማከናወን፣ የአቃቂ የከርሰ ምድር ውኃ በተለያዩ ምዕራፎች በማልማትና በከተማዋ ኪስ ቦታዎች በተቆፈሩ ጥልቅ የውኃ ጉድጓዶች አቅርቦቱን  ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል። - ; ዛሬ በተመረቀውና በቀጣይ ጊዜያት በሚመረቁ ሁለት የውኃ ፕሮጀክቶች በቀን 114 ሺህ ሜትር ኪዩብ ውኃ ማምረት የሚያስችል አቅም ተፈጥሮ ሙሉ ለሙሉ ወደ ሥራ ተገብቷል። ከተማዋ ለኀብረተሰቡ በዕየለቱ የውኃ አገልግሎት ለመስጠት ከ670 ሺ ሜትር ኪዩብ በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን በአሁን ወቅት ግን 350 ሺህ ሜትር ኪዩብ ውኃ ብቻ እያሰራጨ ይገኛል። - ; የተመረቀው የአቃቂ የከርሰ ምድር ውኃ የከተማዋን የውኃ አቅርቦት ወደ 494 ሺህ ሜትር ኪዩብ ከፍ በማድረግና አጠቃላይ የውኃ ሽፋኑን ወደ 70 በመቶ የሚያሳድግ ነው። የአዲስ አበባ የውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አወቀ ኃይለማርያም በበኩላቸው በከተማዋ እየታየ ያለው ሁለንተናዊ ዕድገት በተለይ በውኃው ዘርፍ መሰረታዊ በሚባሉ የውኃ አቅርቦትና ፍላጎት አለመመጣጠን አስከትሏል ብለዋል። - ; እንደ አቶ አወቀ ገለፃ የሚስተዋሉ ችግሮችንም ለመቅረፍ ውኃ በማይደርስባቸው ቦታዎች ላይ በፈረቃና በቦቴ ለማዳረስ ተሞክሯል፤ በተጨማሪም የውኃ ችግሩን ሙሉ ለሙሉ ለማስቀረት ስድስት ፕሮጀክቱ በሁለት ምዕራፎች ሲከናዎን ቆይቶል። - ; በዚህም ዛሬ በተመረቀው በአቃቂ ከርሰ ምድር፣ በለገዳዲ የውኃ ግድብ ማስፋፊያና በተለያዩ የኪስ ውኃ ጉደጓዶች በያዝነው በጀት ዓመት 249 ሺህ ሜትር ኪዩብ ተጨማሪ ውኃ ለማሰራጨት ታቅዷል። - ; በመጀመሪያው ምዕራፍም 114 ሺህ ሜትር ኪዩብ ውኃ ወደ ስርጭት ገብቷል፤ ይህም የከተማዋን ሰሜን፣ ሰሜን ምስራቅና ምዕራብ አካባቢ ነዋሪዎችን የውኃ እጥረት ችግር የሚያቃልል ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። - ; ይሁንና አሁንም ድረስ በከተማዋ የውኃ እጥረት በመኖሩ እጥረቱን በዘላቂነት ለመፍታት ከፍተኛ ርብርብ እተደረገ መሆኑን አስታውቃዋል። - ; የፕሮጀክቱን ግንባታ ለማካሄድ አንድ ዓመት ተኩል የወሰደ ሲሆን ሲ.ጂ.ሲ.ኦ.ሲ በተባለ የቻይና የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ተገንብቷል። - ; እንደ ኢዜአ ዘገባ የገንዘብ ምንጩም ከቻይናው ኤግዚም ባንክ በረዥም ጊዜ ብድር የተገኘ ሲሆን 2 ቢሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል። ),
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
454
ማረት ያስገነባቸው የውሃ ፕሮጀክቶች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ ። ማሀበረ ረዴት ትግራይ ባለፈው የፈረንጆች አመት በክልሉ 21 ወረዳዎች በዘጠኝ ሚሊየን ብር ያስጀመራቸው በርካታ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን አስታወቀ ። በማረት የገጠር መጠጥ ውሃ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ጌታቸው ሃይሌ ትናንት ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማእከል እንደገለጹት ማረት ከአምስት የረዴት ድርጅቶች ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ያስቆፈራቸው 190 የእጅና 54 መካከለኛ የውሃ ጉድጓዶችና 30 የጎለበቱ ምንጮች ካለፈው ወር ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ። እንዲሁም ድርጅቱ ያስጠገናቸው 34 የእጅ ውሃ ጉድጓዶች ፣ 24 ምንጮችና ሁለት የዝናብ ማጠራቀሚያ ገንዳዎች ለአገልግሎት መብቃታቸውን ተናግረዋል ። አብዛኞቹ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የሻእቢያ መንግስት በወረራው ወቅት ከፍተኛ ውድመት ባደረሰባቸው የአህፈሮም ፣ መረብለ የውሃ ፕሮጀክቶቹ ደህንነት ተጠብቆ አገልግሎታቸውን ለማስቀጠል እንዲቻልም ከሀብረተሰቡ የተውጣጡ 1ሺ 686 አባላት ያሏቸው 291 የውሃ አስተዳደርና ቴክኒክ ኮሚቴዎች መቋቋማቸውን ጠቁመው ፤ ለኮሚቴዎቹ አባላት የጥገና ትምህርትና ለአንድ አመት የሚያገለግሉ የመለዋወጫ እቃዎች እንደተሰጧቸው አስታውቀዋል ። የውሃ ፕሮጀክቶቹ በአሁኑ ወቅት ከ98 ሺ የሚበልጡ ነዋሪዎችና ከ7ሺ በላይ እንስሳት የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ በማድረግ ላይ እንደሆኑ ከአቶ ጌታቸው ገለጻ ለመረዳት ተችሏል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
455
በሰቆጣ የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት በአድዋ ደግሞ የውሃ ማጠሪያ ፕሮጀክት ግንባታ መጓተት ቅሬታ ፈጥሯል በዋህግምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ሰቆጣ ከተማ በንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት መቸገራቸውን በከተማው አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በአድዋ የተጀመረው የውሃ ማጣሪያ ፕሮጀክት ግንባታ በመጓተቱ ቅሬታ እንዳሳደረባቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በሰቆጣ ከተማ ማይ የቡሊት አካባቢ ነዋሪ ወይዘሮ ሰላማዊት ታደሰ እንዳሉት በከተማው የሚስተዋለው የውሃ እጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቷል፡፡ በተለይም ባለፈው አንድ ወር የውሃ አቅርቦት አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ” ሁለት ልጆቼን በየእለቱ ጀሪካን አስይዤ ውሃ እንዲቀዱ ስለምልካቸው ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዳይከታተሉ አድርጓቸዋል “ብለዋል፡፡ በከተማዋ የቀበሌ ሁለት ነዋሪ አቶ አበበ ጉደታ በበኩላቸው የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ባለመኖሩ የጉድጓድን ውሃ ለመጠጥነት ለመጠቀም መገደዳቸውን ገልጸው በዚህም እሳቸውና ልጆቻቸው ለበሽታ መደረጋቸውን ተናግረዋል። በየአስር ቀኑ ልዩነት የውሃ አቅርቦቱ ይደርሳችኋል ቢባልም በተባለው ጊዜ ሊደርሳቸው እንዳልቻለ ነው ያመለከቱት፡፡ ወይዘሮ ወይዘር ካሳሁን በሰጡት አስተያየት በቂ የመጠጥ አቅርቦት ባለመኖሩ መቸገራቸውን ገልጸዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ አብርሃም አሰፋ ስለጉዳዩ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ “ለከተማዋ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚሰጠው ጥልቅ ጉድጓድ ከተገነባ 10 ዓመታት መሆኑ የማመንጨት አቅሙ እየቀነሰ ነው “ብለዋል። በዚህም ቀደም ጉድጓዱ በሰከንድ 15 ሊትር ይሰጥ እንደነበረ አሁን ላይ ወደ 4 ሊትር ዝቅ ማለቱን ጠቁመው የተጠቃሚው ቁጥርም ከ19 ሺህ ወደ 35 ሺህ ከፍ በማለቱ ጭምር እንደሆነ አመልክተዋል። ችግሩን በጊዜያዊነት ለመፍታት አቅርቦቱ በፈረቃ ለህብረተሰቡ እየቀረበ መሆኑን ጠቅሰው “ተጨማሪ በአንድ ሚሊዮን 800ሺህ ብር ብር ወጪ ስምንት አነስተኛ የእጅ ጉድጓዶች በመገንባት ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል “ብለዋል፡፡ የውሃ ጉድጓድ ላላቸው ግለሰቦችም በነፃ የውሃ ማከሚያ ኬሚካል በየወሩ እየተሰራጨላቸው እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ የከተማዋን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት በዘላቂነት ለመፍታትም የዲዛይን ስራ እየተከናወነ መሆኑን አቶ አብረሃም ጠቁመዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ለአድዋ ከተማና አካባቢው ነዋሪ ህዝብ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን በሶስት እጥፍ ያሳድጋል ተብሎ ግንባታውን የተጀመረው ” የምድማር” የውሃ ማጣሪያ ፕሮጀክት እስካሁን ባለመጠናቀቁ ቅሬታ እንዳሳደረባቸው ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ ገብረመስቀል ልዑል ለኢዜአ እንዳሉት የውሃ ማጣሪያ ፕሮጀክቱ በተያዘው ዓመት መጀመሪያ ላይ ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚሰጥ ቢነገረንም ግንባታው እስካሁን አላለቀም። “በወቅቱ ባለመጠናቀቁ በተደጋጋሚ የህበረተሰቡ ጥያቄ ሆኖ ቆይቷል” ያሉት አቶ ገብረመስቀል፣በአድዋ ከተማ ተደጋጋሚ የመጠጥ የውሃ መቆራራጥ እያጋጠመ መቸገራቸውን ገልጸዋል። በአካባቢው በቂ የውሃ ሃብት እያለ የማጣሪያ ፕሮጀክቱ ባለመጠናቀቁ ውሃ በፈረቃ ተደርጉ ውሀ የሚያገኙት እስከ አራት ቀናት ቆይቶ ነው፡፡ ችግሩን እየበረታ በመምጣቱ ሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሔ እንዲያመቻችላቸው የሚፈልጉ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡ በከተማው በተፈጠረው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት መቆራረጥና እጥረት ምክንያት መቸገራቸውን የተናገሩት ደግሞ የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ አወጣሽ ገብረኪዳን ናቸው። አሁንም የሚመለከተው አካል የተጀመረውን ፕሮጀክት አጠናቆ ተገቢ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ሰጥቶ መሰራት እንዳለበትም አመልከተዋል፡፡ የዓድዋ ከተማ ውሃና ፍሰሽ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን ገብረእግዚአብሔር ስለጉዳዩ ተይቀው በሰጡት ምላሽ “የፕሮጀክቱ ሲቪል ስራዎች ተጠናቆ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎች ባለመጠናቀቁ ተጓቷል” ብለዋል። የውሃ ማሰራጫ ቱቦ የመዘርጋትና በከተማው አስተዳደር አቅም የሚከናወኑ ሌሎች ስራዎችን መጠናቀቀቸውንም ገልጸዋል። የውሃ ማጣሪያ ፕሮጀክቱ አካል የሆነው የኤሌክትሮሜካኒካል ስራው በቀጣዩ ዓመት መጀመሪያዎች ወራት ላይ ተጠናቅቆ አገልገሎት መስጠት እንደሚጀምር ከትግራይ ክልል ውሃ ሃብት ቢሮ እንደተገለጻላቸው ተናግረዋል። የክልሉ ውሃ ሃብት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ፍትዊ ግደይ በበኩላቸው ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ የኤልክትሮ መካኒካል እቃዎች በሃገር ውስጥ ገበያ እንደሌሉና ከውጭ ለማስገባት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የእቃዎቹ የግዥ ሂደት እንደተጀመረና የገቢ እቃዎች በዶላር ዋጋ ጭማሪ ምክንያት በተፈለገው ጊዜ ሊገኝ አለመቻሉንም ጠቁመዋል። ” በዚህ ምክንያትም ፕሮጀክቱ በዚህ ጊዜ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ብሎ ለመናገር አስቸጋሪ ነው” ያሉት ኃላፊው፣ ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ፕሮጀክቱ የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በመደበው 300 ሚሊዮን ብር ወጪ ነው እየተገነባ የሚገኘው። እስከ አሁን ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ ግንባታ 75 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያ ላይ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ባለፈው ዓመት የካቲት ወር ላይ የኢዜአ ሪፖርተር ዘግቦ እንደነበር ይታወሳል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
456
በጋምቤላ ክልል የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽ ለማደረግ እየተሰራ ነው ጋምቤላ መጋቢት 17/2010 በጋምቤላ ክልል የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽ ለማደረግ ከ63 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የ146 የውሃ ተቋማት ግንባታ በመካሄድ ላይ መሆኑን የክልል ውሃና መስኖ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ። ግንባታቸው በመካሄድ ላይ ያሉት የውሃ ተቋማት ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ሲጀመሩ ከ107 ሺህ በላይ ህዝብ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ይሆናል ተብሏል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ኡጎቶ አደንግ ለኢዜአ እንደገለጹት የውሃ ተቅማቱ ግንባታ በመካሄድ ላይ ያለው በክልሉ 13 ወረዳዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ባልተዳረሰባቸው የገጠር ቀበሌዎችና ዘጠኝ የወረዳ ከተሞች ነው። በገጠር ቀበሌዎች እየተገነቡ ከሚገኙት የውሃ ተቀማት መካከል 137 ጥልቅ፣ መለስተኛ ጥልቅ፣ እጅጅ ውሃ ጉድጓዶችና የምንጭ የማጎልበት ስራዎች ናቸው፡፡ በዘጠኝ የወረዳ ከተሞች ደግሞ አዲስ የንፁህ መጠጥ ውሃና የማስፋፊያ ግንባታ ስራዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል፡፡ በወረዳ ከተሞች ግንባታ እየተካሄደባቸው ከሚገኙት መካከል የኝንኛንግ፣ የኳቲያንግ፣ የአቦል፣ የፉኝዶ፣ የሜጢና ሌሎችም ከተሞች እንደሚገኙበት ተናግረዋል። እየተገነቡ ከሚገኙት የውሃ ተቅማት መካካልም ከአራቱ በስተቀር ሌሎቹ በተያዘው በጀት ዓመት መጀመራቸውን የገለጹት ኃላፊው ፕሮጀክቶቹ እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ተጠናቀው አገልግሎት እንዲጀምሩ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም በገጠር ቀበሌዎች የውሃ ተቋማት ተደራሽ ካለመሆን ጋር ተያይዞ በህብረተሰቡ ላይ እየደረሰ ያለውን የጤና ችግርና ከከተሞች መስፋፋት ጋር ተያይዞ እየተፈጠር ያለውን የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት ለማቀለል ቢሮው ከመቸውም ጊዜ በበለጠ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል። በበጀት ዓመቱ እየተገነቡ ያሉት የውሃ ተቋማት ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቁም ከ107 ሺህ በላይ የገጠርና የከተማ ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ አገልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ አሁን ያለውን 64 ከመቶ የክልሉን የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ወደ 84 ከመቶ ለማሳደግ እንደሚያስችል ገልፀዋል፡፡ "በከተማው የውሃ ችግር በመኖሩ ለግማሽ ቀን ያህል የቤት ስራየን ትቼ ተራ በመያዝ ውሃ በመፈለግ ነው ጊዜየን የማሳልፈው" ያሉን ደገሞ የአቦል ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ኝኬዎ ቻም ናቸው። ስለሆነም በቅርቡ ተጀምሯል የተባለው የውሃ ተቋም በፍጥነት ተጠናቆ የአገልግሎቱ ተጠቀሚ የሚሆኑበት ሁኔታ እንደመቻችላቸው ጠይቀዋል። የዚሁ ከተማ ነዋሪ አቶ ቶለሳ አሰፋ በሰጠው አስተያየት ንግድ ስራቸውን ትተው ውሃ ለማግኘት ወረፋ በመያዝ ከአምስት ስዓት በላይ እንደሚጉላሉ ገልጸዋል። በጎግ ወረዳ የአቴቲ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ሜሪ ኡጁሉ በሰጡት አሰተያየት በቀበሌያቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ባለመኖሩ የኩሬ ውሃ ለመጠቀም መገደዳቸውን ተናግረዋል። የክልሉ ውሃና መስኖ ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊው በአቦል ከተማና በአቴቲ ቀበሌ ያለውን የንጽህ መጠጥ ውሃ ችግር ተጨማሪ የውሃ ተቋማትን በመገንባት እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ባለው ጊዜ ይፈታል ብለዋል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
457
የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ፌዴሬሽን ምስረታ በ'የዓለም ውሃ ቀን' ዋዜማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ፌዴሬሽን ምስረታ በ'የዓለም ውሃ ቀን' ዋዜማ አየለ ያረጋል/ኢዜአ የኢትዮጵያ ከተሞች በዓለም ውሃ ቀን ዋዜማ (ትናንት) በመሰረቱት 'የኢትዮጵያ ከተሞች የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ፌዴሬሽን' ለሕዝብ ቅሬታ ምንጭ ለሆነው የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ዘርፍ መሻሻል ተስፋ ይዘው መጥተዋል። ዛሬ መጋቢት 13 ቀን 2010 ዓ.ም የ'ዓለም የውሃ ቀን' ነው። ውሃ ለሕይወታዊያን ፍጥረታት ስሪት ትልቁ ግብዓት ብቻ አይደለም፤ ለህልውናቸው ብርቅዬ ስጦታ ጭምር እንጂ፤ በተለይ ለሰው ልጆች (70 በመቶ የውሃ ስሪቶች) ለመጠጣችን፣ ለውበታችን፣ ለጤናችን፣ ለተዝናኖታችን ዋስትና ነው። የምድራችን የውሃ ሀብት ክምችት የተትረፈረፈ ቢሆንም አብዛኛው ለመጠጥነት የማይውልና የብክለት ሰለባ ነው። በአየር ንብረት ለውጥ፣ የአካባቢ ብክለት፣ በከተሞችና ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት፣ የሕዝብ ብዛት በሰው ልጆች ውድ ስጦታ 'ውሃ ሀብት' ላይ ትልቅ ስጋት መደቀኑ አልቀረም። እናም የቅርብ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አንድ ቢሊዮን የሚገመቱ ሰዎች ንጹህ የመጠጥ ውሃ ይጠማሉ። የ'ውሀ ማማ' በምትባለው የምድረ ቀደምቷ አገር ኢትዮጵያም የንጹህ መጠጥ ውሃ ነፍስ ወከፍ ድርሻቸው ከሚፈለገው በታች የሆነባቸው ሰዎች ቁጥር ቀላል አይደለም። በኢትዮጵያ 30 በመቶ ህዝብ ለንፁህ መጠጥ ውሃ፣ 70 በመቶ ደግሞ ለፍሳሽ አገልግሎት ተደራሽ አይደለም። ከገጠሩ ይልቅ የተሻለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ባለባቸው ከተሞች አካባቢ እንኳን የውሃ አቅርቦት ሰፊ የሕዝብ ቅሬታ ምንጭና የማኅበራዊ ቀውስ መንስኤ ሆኗል። እናም አብዛኛዎቹ የአገሪቷ ከተሞች የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የጥራትና የተደራሽነት ማነቆ ተጋርጦባቸዋል። አገልግሎት ሰጭ ተቋማትም 'ለችግሩ መፍትሔነት ማኅበር መስርተን እንስራ' በሚል በትናንትናው ዕለት በክልሎች የሚገኙ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ማኅበራት የተውጣጡ 55 ከተሞች 'የኢትዮጵያ ከተሞች የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ፌዴሬሽን' የተሰኘ ማኅበር መስርተዋል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ አባል ከተሞችም ለሕዝብ ቅሬታ ምንጭ ለሆነው የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎትን "ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ፣ ዘላቂና አስተማማኝ አገልግሎት ለመዘርጋት ያግዘናል" የሚል ተስፋ ጥለውበታል። በውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር የመስኖ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ገርባ ''የከተሞች ህዝብ ጨምሯል፣ ኢንዱስትሪ ተስፋፍቷል፣ ይህም የኅብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ፍላጎቱ አንሮታል፤ ከአቅርቦቱ ጋር አልተጣጣመም። እናም የውሃ ሀብትን መለየት፣ ማልማትና መንከባከብ የማይቆም ቀጣይ ስራ ነው'' ይላሉ። ፌዴሬሽን መመስረቱ ሁሉንም ነገር ባይሰራም በዘርፉ ወደሚፈለገው ደረጃ ለመድረስ ከተናጠል ይልቅ በቡድን መስራቱ ይበልጣል፤ ለአብነትም ለኢንቨስትመንት የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለማሟላት በተደራጀ መልኩ ለመስራት ያግዛል ባይ ናቸው። ተቋማቱ በተናጠል የውድድር ስሜት እንዲፈጥሩ የራሱን እገዛ እንደሚያደርግ ነው የሚገልጹት። 'ሌላውና ዋናው የፌዴሬሽኑ ዓላማ ግን ወዲህ ነው' ይላሉ። የፌዴሬሽኑ አንዱ ዓላማ አቅርቦትና ፍላጎቱ ላልተጣጣመው የውሃ አገልግሎት ዘርፍ ችግርን መፍትሄ ለማምጣት ትልቅ ካፒታል ይጠይቃል። መንግስት ለውሃ ልማት የሚያደርገው የኢንቨስትመንት ወጪ እያደገ ቢመጣም የህብረተሰቡን ፍላጎት መመለስ አልቻለም። ስለዚህም ከፌዴሬሽኑ መመስረቻ ዓላማዎች መካከል አንዱ "የግሉ ዘርፍ እንዲሳተፍ ምቹ ሁኔታን መፍጠር" የሚል ነው። የግሉን ዘርፍ ለማሳተፍ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ግቦች ቢቀመጡም "እስካሁን ግን በከተማ በውሃ ልማት ዘርፍ በጥናት፣ በተቋራጭና ዲዛይን ስራዎች ከነበረው አገልግሎት በዘለለ የውሃ ልማት አልምቶ ለህብረተሰቡ ወይም ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት የመሸጥ ስራ አልነበረውም" ይላሉ። ስለሆነም መንግስት በገጠርና በከተማ ብቻውን ያለውን ፍላጎት ማርካት ስላልቻለ የግሉን ዘርፍ እምቅ አቅም ለመጠቀም ማሳተፍና ማጎልበት ማስፈለጉን ያስረዳሉ። እናም በቀጣይ፤ የግሉ ዘርፍ የውሃ ጉድጓድ ቆፍሮ ለአንድ መንደር አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል። በቀጥታ ለተጠቃሚው ባያከፋፍልም እንኳን የውሃ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ ለከተሞች የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ተቋማት የሚሸጥበት እድል ይኖራል። ከታሸገ ውሃ አቅርቦት በተጨማሪ በቧንቧና ሌሎች ግብዓት አቅርቦቶች አቅምን በማሳደግ በትላልቅ የውሃ ጋኖች ማቅረብ ይችላል። "መንግስትም አሰራሩን የህግ ማዕቀፍ በማውጣት፣ ልምድ በማምጣትና ቴክኖሎጂ በማሰባሰብ ያግዛል" ብለዋል። በኦሮሚያ ክልል የዱከም ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ስራ እስኪያጅ አቶ አህመድ አብዱልጀሊል ማህበሩ" በጣም ብዙ ተስፋ አለው" ይላሉ። ትልቁ ተስፋ መንግስት በውሃ ዘርፍ አሰራሮች ላይ ፖሊሲ ሲቀርጽ ፌዴሬሽኑ ስለሚሳተፍ እንደየአካባቢውና ወቅቱ ነባራዊ ሁኔታ የተጣጣሙ የፖሊሲ ሃሳቦችን ለማመንጨት እድል ይፈጥራል። በውሃ ሀብት ላይ ከተመሰረቱ የተፋሰስ ባለስልጣኖች ጋር በቅንጅት ለመስራት አጋጣሚ ይፈጥራል። "የውሃ አጠቃቀምን፣ የመልካም አስተዳደር ችግርን፣ የውሃ ብክለትን እነዚህ ሁሉ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮ ለመውሰድ የተመሰረተ ነው" ብለዋል። በትግራይ ክልል የአክሱም ከተማ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ሥራ እሰኪያጅ አቶ መስፍን ብሩ ፌዴሬሽኑ አገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ የሚሰሩትን በጥራትና በአቅርቦት በተለይ አሁን ባለው በቴክኖሎጂ በተደራጀ አኳሃን ያለባቸውን ችግር ለመፍታት፣ በግላቸው የሚሰሩትን የተደራጀ አቅም ፈጥሮ ለማከናወን፣ ውሃ አገልግሎቶችም እርስ በርሳቸው እንዲተዋወቁ እንደሚያደርግ ያላቸውን እምነት ይገልጻሉ። ከሃረሪ ክልል ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የተወከሉት አቶ ቡሽራ መሃመድ ፌዴሬሽኑን ለመመስረት ከ10 ዓመታት በፊት መወሰኑን ያስታውሳሉ። በፎረም ደረጃ ቆይቶ ከረጅም ጊዜ በኋላ ዘንድሮ መመስረቱን ይበል አሰኝቷቸዋል። ፌዴሬሽኑም ለተቋማቱ የአገልግሎት ልህቀት ማዕከልነት፣ አገልግሎታቸው እንዲዘምንና በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ፣ የተቀላጠፈና ደንበኛን የሚያረካ ለማድረግ ያስችላል የሚል ተስፋ አላቸው። "የውሃ ዘርፍ ለመልካም አስተዳደር፣ ለማህበራዊ ቀውሶች፣ ለጤና፣ ለልማት መሰረት ነው" የሚሉት አቶ ቡሽራ፤ ለዕለታዊ ቁልፍ ሚና ለሚጫወተው ውሃ ሀብት በሚፈለገው ደረጃ ለመገኘት የተበጣጠሰውን አሰራር በቅንጅት ለመምራት፣ መልካም ተሞክሮዎችን ለማስፋት ሚናው የጎላ ነው። በአዲስ ለተመሰረተው ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት የመቀሌ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጊደና አበበ "የፌዴሬሽኑ መመስረት አብይ መነሻ ጉዳይ በህዝባችን ላይ ያለው የመልካም አስተዳደር ችግር በተለይ ከውሃ አቅርቦት ጋር በተያያዘ የጥራት፣ የግልጽነትና የተነሳሽነት ችግር ያለበት በመሆኑ ነው። ይህን አገልግሎት ግልጽና ፈጣን ከማድረግ አኳያ ጥረቶች አሉ። ስለሆነም አቅም ለማደራጀትና ተግባር ላይ ለማዋል ፌዴሬሽኑ ይረዳል" ብለዋል። ውሃ ከምንጩ ጀምሮ ተጠቃሚው ጋር እስኪደርስ ቴክኒካዊ፣ መልካም አስተዳደራዊና ህጋዊ ችግሮች እንደሚያጋጥሙት ያብራራሉ። በፕሬዚዳንትነት ዘመናቸውም የአጭር፣ መካከለኛና የረጅም ጊዜ ዕቅዶችን በማውጣት ለመስራት መዘጋጀታቸውን ይገልጻሉ። በተለይም የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለው ችግር በአጭር ጊዜ መፈታት እንዳለበት ያምናሉ። መልካም ተሞክሮዎችን ማስፋት፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ማስተዋወቅ፣ አቅምን ማጠናከርና መደገፍ፣ ከህግም አኳያ የተሻለ ማዕቀፍ እንዲኖር በርግጠኝነት የተሻለ ስራ እንዲሰራ እንደሚያግዝ አብራርተዋል። ተቋማቱ ተናበው በመስራትም የወጪ ብክነትን ለመቀነስ እገዛ እንደሚያደርግ ነው አጽንኦት የሰጡት። የዓለም የውሃ ቀን 'ተፈጥሮ ለውሃ' ወይም 'ተፈጥሮን በመንከባከብ የውሃ ተግዳሮትን መፍታት' በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ተከብሯ። ሚኒስትር ዴኤታው ከበደ ገርባ የውሃ ቀን በተለያዩ ውይይቶች ሲከበር ተፈጥሮን መንከባከብ፣ ውሃን በቁጠባ በመጠቀም ከብክነት የመከላከልና የመጠበቅ ስራዎች በስፋት መሰራት እንዳለባቸው "ግንዛቤ በመፍጠር ነው" ብለዋል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
458
በአንዳንድ የአዲስ አበባ አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ እጥረት ነዋሪዎችን እያማረረ ነው በአንዳንድ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ከሁለት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመጠጥ ውሃ እጥረት ነዋሪዎችን እያማረረ ነው፡፡ ዋልታ ቴሌቪዥን ምልከታ ባደረገባቸው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04፣ ጎተራ እና የሳሪስ አዲስ ሰፈር ነዋሪዎች በውሃ እጦት እንደተቸገሩና ለአላስፈላጊ ወጪ መዳረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ በጎተራ የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች እንደገለጹት ላለፉት ሁለት አመታት በቀን ውሃ ሳያገኙ እንደቆዩ ጠቁመው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ሙሉ በሙሉ መቋረጡን አስረድተዋል፡፡ በመሆኑም ለአንድ ጀሪካን ውሃ እስከ 40 ብር ድረስ ወጪ ለማወጣት መገደዳቸው እንዳማረራቸው ጠቁመዋል፡፡ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ነዋሪዎች በበኩላቸው አካባቢያቸው ለአንዳንድ የመሰረተ ልማት ግነረባታዎች በሚቆፈርበት ወቅት ሲባክን የሚመለከቱት ውሃ ወደ ቧንቧቸው ሊመጣ አለመቻሉ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል፡፡ የከተማው ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በበኩሉ የውሃ እጥረቱ እንዳለ አምኖ ግዜያዊ መፍትሄ ይሆን ዘንድ ንጹህ የመጠጥ ውሃ በቦቴ ለነዋሪዎቹ ለማድረስ ቃል ገብቷል፡፡ በባለስልጣኑ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት መሪ አቶ እስጢፋኖስ አስራት እጥረቱ የተከሰተው በፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን መሆኑን ጠቁመው እጥረቱን በዘላቂነት ለመፍታት ትልልቅ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ነው ብለዋል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
459
 የውሃ እጥረት የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን እያማረረ ነው በአዲስ አበባ የንጹህ መጠጥ ውሃ ስርጭት መቆራረጥ ነዋሪዎችን እያማረረ መሆኑ አስተያየት ሰጪዎች ተናገሩ። በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን የእቅድ ዘመን 58 በመቶ የነበረውን የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን እስከ 2012 ዓ.ም 83 በመቶ ለማድረስ እቅድ ተይዟል። በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ በከተማና በገጠር ያለው የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን 67 በመቶ መድረሱን የውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። የከተማውን ህብረተሰብ ንፁህ፣ በቂ እና ዘላቂ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት በቀን ከ40 ሊትር እስከ 100 ሊትር ለማድረስ እቅድ ቢያዝም በቀን 10 ሊትር ውሃ አጥተው የሚንገላቱ ነዋሪዎች በከተማዋ ሞልተዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ነዋሪ የሆኑት አቶ በድሩ ሙሀመድ፣ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በአካባቢያቸው ለአንድ ወር ያህል ውሃ በመጥፋቱ ህይወትን ለመምራት ተቸግረዋል። ሁሉም እንቅስቃሴ ከውሃ ጋር በሆነበት ከተማ አንድ ወር ሙሉ ያለ ውሃ ተቀምጠናል፤ ‘ብሶታችንን ሰምቶ ምላሽ የሚሰጠን አካልም አጥተናል’ ብለዋል። ምግብ አብስለው ለመብላት፣ መጸዳጃ ቤት ለመጠቀም፣ ለመጠጥ የሚሆን የታሸገ ውሃ በመግዛት ለተጨማሪ ወጪ መዳረግ ለከፍተኛ ችግር ያጋለጣቸው መሆኑን የሚናገሩት ነዋሪዎች የሚመለከተው አካል መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ወይዘሮ ባዩሽ ተሰማ፣ ‘ችግሩ የከፋ ደረጃ ላይ ከመድረሱ በፊት ቆም ብሎ ሊያዬን ይገባል’ ብለዋል። ሌላዋ ያአካባቢው ነዋሪ ወይዘሮ አለምነሽ አሰፋ “ይሄንን ችግር መንግስት እንዲያይልን በሳምንትም በ15 ቀንም ቢሆን የሆነ መፍትሄ ይፈልግልን” ነው ያሉት፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በበኩሉ ችግሩ በተባለው መጠን ባይሆንም በመብራት መቆራረጥና በመሰረተ ልማት ግንባታዎች ምክንያት የውሃ ስርጭቱ እንደሚቋረጥ ገልጿል። የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት መሪ አቶ እስጢፋኖስ ብስራት በከተማዋ ያለውን የውሃ አቅርቦት ግምት ውስጥ በማስገባት ውሃ በፈረቃ መጠቀም የተለመደ እንደሆነ ተናግረዋል። ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በተስማማው መሰረተ መብራት በሚጠፋበት ወቅት ኅብረተሰቡ አውቆ ዝግጅት እንዲያደርግ በመገናኛ ብዙሃን እንደሚነገር ጠቁመዋል። መብራት በድንገትና በተደጋጋሚ በመጥፋቱና በመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታ ምክንያት ላለፉት ሶስት ሳምንታት ውሃ እየተቆራረጠ መሆኑን ገልጸዋል። በከተማዋ አንድ ወር እና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ውሃ የጠፋባቸው አካባቢዎች ካሉ ለቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አመልክተው ምላሽ ካላገኙ በ906 የስልክ መስመር ወይም ዋናው መስሪያ ቤት በአካል መጥተው ማመልከት እንደሚችሉ ገልጸዋል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
460
በአማራ ክልል ያለውን አሳሳቢ የጽዳት ጉድለትና የንጹሕ ውሃ አቅርቦት እጥረት ለማቃለል ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው ተገለጸ፡፡ በደብረብርሃን ከተማ እየተካሄደ ባለው የውይይት መድረክ ላይ በአለም የውሃና የአካባቢ ጽዳት ኘሮግራም [ደብሊው ኤስ ፒ የአማራ ከልል ጤና ጥበቃ ቢሮ አማካሪ የሆኑት አቶ ከበደ ፋሪስ እንደገለጹት ውይይቱ በክልሉ ውስጥ ባለው አሳሳቢ የግልና የአካባቢ ጽዳት ጉድለትና የንጹህ ውሃ አቅርቦት ችግር ላይ በጥልቀት በመነጋገር የአጭርና የረጅም ጊዜ የቴሌቪዥን ኘሮግራም ማሰራጨት ችግሩን ለመቀነስ ያስችላል፡፡ ችግሩን ለማቃለል ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ከሕብረተሰቡ ጋር በመሆን ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸውም አቶ ከበደ አስገንዝበዋል፡፡ ይህን ኘሮግራም ለማዘጋጀት በክልሉ ውስጥ ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች የተውጣጡ ግብረኃይሎች፣ የሀይማኖት ተቋማት፣ የሚመለከታቸው አካላትና ሕብረተሰቡ ቀጥተኛ ግንኙነት በመመስረት በጋራ ለችግሩ መፍትሄ የሚሹበት ሁኔታ ይመቻቻል ብለዋል፡፡ የውይይት መድረኩ የተዘጋጀው ከአለም የውሃና የአካባቢ ጽዳት ኘሮግራም ጋር በመተባበር እንደሆነ የገለጹት አማካሪው ከወይይቱ በኋላም እያንዳንዱ አጋር ድርጅት ከማህበረሰቡ ጋር ስለጉዳዩ አሳሳቢነት በመነጋገር በቅንጅት መስራት የሚቻልበትን ሁኔታ እንደነሚያመቻቹ አቶ ከበደ ተናግረዋል ፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
461
በባሌ ዞን በዶሎ መና ከተማ የመጠጥ ውሃ እጥረት በማጋጠሙ ለውሃ ወለድ በሽታዎች መጋለጣቸውንና አገልግሎቱም ከሕብረተሰቡ ቁጥር ጋር ባለመመጣጠኑ መቸገራቸውን የከተማው ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ ከነዋሪዎቹ አንዳንዶቹ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስረዱት አገልግሎቱ ከዚህ ወር መግቢያ አንስቶ በሳምንት አንድ ጊዜ ብቻ እንዲዳረስ በመደረጉ የወንዝና የኩሬ ውሃ በመጠቀም ለበሽታ በመዳረግ ላይ ናቸው፡፡ በከተማው አገልግሎቱን ሲሰጡ የነበሩ ቦኖዎች ካለፈው ዓመት ጀምሮ ስራ በማቋረጣቸው ችግሩ እንዲባባስ ማድረጉንም አመልክተዋል፡፡ የከተማው የቧንቧ ውሃ ከ20 ዓመታት በፊት ለ5 ሺህ ነዋሪዎች አገልግሎት እንዲሰጥ የተሰራ ቢሆንም እያደገ ከሄደው የነዋሪዎች ቁጥር ጋር ሊመጣጠን ባለመቻሉ ችግሩ ማጋጠሙን አስረድተዋል፡፡ በከተማው የሚገኙ የጤና ድርጅቶች በአብዛኛው የሚከታተሉት በውሃ ወለድ በሽታዎች የተያዙትን ህሙማን በመሆኑ ችግሩ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መፍትሄ እንዲሰጠውም ነዋሪዎቹ አሳስበዋል፡፡ የዶሎመና ከተማ ሹም አቶ ጀማል አብዶ ችግሩን ለማቃለል ለዞኑ ውሃ ሀብት ጽህፈት ቤትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አሳውቀው ምላሽ እየጠበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የባሌ ዞን ውሃ ጽህፈት ቤት ተወካይ አቶ ብርሃኑ በላቸው በበኩላቸው የከተማዋ የውሃ ችግርን ለማቃለል 7 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግና የኦሮሚያ ክልል ውሃ ልማት ቢሮም በጀቱን በማፈላለግ ላይ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
462
በባሌ ዞን ድሬ ሼክ ሁሴን አካባቢ በ20 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመጠጥ ውሃ ተቋም ተገቢውን አገልግሎት ስለማይሰጥ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ አንዳንድ ነዋሪዎች ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት መንግስት የአካባቢውን የመጠጥ ውሃ ችግር ለማቃለል ከአንድ ዓመት በፊት ያስገነባው ተቋም ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት ባለመጀመሩ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ለማግኘት አልቻሉም፡፡ በችግሩም የተነሳ ላለፉት ስምንት ወራት የጉድጓድ ውሃ በመጠቀም ለውሃ ወለድ በሽታዎች መዳረጋቸውንና በተለይ በዓመት ሁለቴ በሚከበረው የዚያራና ሀጂ በዓል ለመሳተፍ የሚመጡ የውጪና የአገር ውስጥ ቱሪስቶች በችግሩ ሳቢያ በአካባቢው ለመቆየት አለመቻላቸውን አስረድተዋል፡፡ የባሌ ዞን ውሃ ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት ተወካይ አቶ ብርሃኑ በላቸው ተጠይቀው ችግሩ የተከሰተው አንዳንድ ሰዎች ቧንቧዎች ላይ ባደረሱት ጉዳት፣ በቴክኒክ ብልሽትና ውሃውን ለሚገፋው መሣሪያ የሚያስፈልገው ነዳጅ እጥረት በማጋጠሙ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በሰዎች ጉዳት የደረሰባቸው ቧንቧዎች በመጠገን ላይ መሆናቸውንና የነዳጅ እጥረቱን ለማቃለል ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ውሃ ሀብት ቢሮ ተጨማሪ በጀት መጠየቁን ተናግረዋል፡፡ በውሃ መስመሩ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሰዎችን ለህግ አሳልፎ መስጠት እንዲቻልና በውሃ መስመሩ ላይ ተገቢው ጥበቃና እንክብካቤ እንዲደረግ ለኅብረተሰቡ ትምህርት በመሰጠት ላይ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
463
በሀገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውሃ የማዳረስ ግብን ለማሳካት ባለድርሻ አካላት ተሳትፏቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ተመለከተ በሀገሪቱ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለማዳረስ የተያዘውን የልማት ግብ ለማሳካት ባለድርሻ አካላት ተሳትፏቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ተመለከተ፡፡ በተቀናጀ ዘላቂ የልማት ግቦች የአካባቢ ንፅህናና የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትና አቅርቦት እቅድ ማሳካት በሚቻልበት ላይ የተዘጋጀ አውደ ጥናት በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ። የውሃ ፣መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስር ዴኤታ ወይዘሮ እቴኔሽ መኩሪያ እንደገለጹት በሀገሪቱ የተቀናጀ ዘላቂ የልማት ግብ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ወዲህ በአካባቢ ንፅህናና ንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት ላይ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል። በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ተግባራዊ በሆነባቸው ባለፉት ሁለት ዓመታት በሀገሪቱ በከተማና በገጠር የንፁህ መጠጥ ውሀ ሽፋን 67 በመቶ ደርሷል፡፡ "በተቀመጠው የልማት ግብ መሰረት በገጠር በቀን አንድ ሰው ማግኘት ያለበትን 25 ሊትር ውሃ ማሳካት ተችሏል" ብለዋል። "በአንድ ኪሎ ሜትር ስፋት የውሃ አቅርቦት እንዲኖር አድርገናል" ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ ባለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል ከ12 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በገጠርና በከተማ ንፁህ መጠጥ ውሃ ማግኘታቸውን ገልፀዋል። በቀጣይ ሁለት ዓመታት የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋኑን 80 በመቶ ለማድረስ የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል። በዘርፉ የገንዘብ፣ የእውቀትና የስራ ተቋራጮች አቅም ማነስ ማነቆዎችን ለመፍታት በቅንጅት መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል ። "ማነቆዎችን ለመፍታት ከዓለም ባንክ፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ከሌሎች ዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶችና አጋሮች ጋር በቅንጅት ይሰራል " ብለዋል ። ሚኒስትር ዴኤታዋ እንዳሉት ጅማ፣ ሐዋሳ፣ መቀሌ፣ ድሬደዋና ጎንደርን ጨምሮ በ20 ከተሞች የተጀመሩ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ አብዛኛዎቹ ተጠናቀዋል። የደንቢ ዶሎ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሀ ተቋም ግንባታ በመጪው ዓመት እንደሚጠናቀቅም ጠቅሰዋል ። በገጠርና በከተማ በግንባታ ላይ የሚገኙት ቀሪዎቹ ስራዎች ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ ነው ተብሏል፡፡ በመንግስታቱ ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የዘላቂ ልማት ፖሊስና እቅድ አማካሪ ሚስትር ፍራንሲስ ፎርቴር በበኩላቸው ኢትዮጵያን ጨምሮ በአስር የዓለም ሀገራት ለንፁህ መጠጥ ውሃ ማስፋፊያ፣ ለኃይል አቅርቦትና ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ለሚከናወኑ ተግባራት ማስፈፀሚያ 80 ሚሊዮን ዶላር ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል ። በተቀናጀ ዘላቂ የልማት ግቦች የአካባቢ ንፅህናና የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትና አቅርቦት እቅድ ለማሳካት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎን ማጠናከር በሚቻልበት ሂደት ላይ ባተኮረው አውደ ጥናት ከትላንት ጀምሮ እንደቀጠለ ነው፡፡ ከአፍሪካና ከሌሎች ዓለም ሀገራት የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት በአውደ ጥናቱ እየተሳተፉ ነው።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
464
በውሃ እጥረት ለከፋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋልጠናል----የሸንዲ ከተማ ነዋሪዎች በምዕራብ ጎጃም ዞን ሽንዲ ከተማ የሚስተዋለው የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኪኖሚያዊ ችግሮች እያጋለጣቸው መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። የሽንዲ ከተማ ውሃ አቅርቦት እጥረትን ለመፍታት በ70 ሚሊዮን ብር በጀት ተግብራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩንም ተጠቁሞል። የከተማው ነዋሪ አቶ አብየ አድማስ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በከተማዋ የውሃ አቅርቦት ሙሉ በሙሉ የለም ማለት ይቻላል። በውሃ አቅርቦት እጥረት ከተማዋን በተሻለ ማልማትና ማሳደግ የሚችሉ የአካባቢው ተወላጅ ባለሃብቶች በውሃ እጥርት ምክንያት አካባቢውን እየለቀቁ መሄዳቸውንም ተናግረዋል። የውሃ እጥረቱ ሕብረተሰቡ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እየተጋለጠ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አብየ፣ በጤና ተቋም የሚወልዱ እናቶችም ለመታጠቢያ የሚሆን ውሃ ከቤታቸው እንዲያመጡ በመደረግ ላይ መሆኑን ገልፀዋል። “ሴቶች የወንዝ ውሃ ፍለጋ ለሰዓታት እንግልት እየደረሰባቸውና አላስፈላጊ ድካም እየደረሰባቸው ነው” ያሉት ደግሞ ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ ሃብታሙ አለማየሁ ናቸው። በሳምንት አንድ ቀን ለ30 ደቂቃ ብቻ የቧንቧ ውሃ እንደምትመጣ አመልክታ፣ አንዳንድ ጊዜ ብልሽት ሲገጥም እስከ አንድ ወር ውሃ የማይገኝበት አጋጣሚ እንዳለ አመልክተዋል። የውሃ እጥረቱ በጤና ተቋማት የሚወልዱ እናቶችና በትምህርት ቤት የሚማሩ ታዳጊ ልጆች ውሃ ይዘው እንዲመጡ መገደዳቸውንና ለከፋ ችግር እየተጋለጡ በመሆናቸው ቅሬታ እንደፈጠረባቸው ገልፀዋል። በችግሩ ምክንያት ከአካባቢያቸው 17 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ቡሬ ከተማ በመሄድ ለአንድ ጀሪካን እስከ 15 ብር አውጥተው ለመግዛት መገደዳቸውን ጠቁመዋል። የውሃ አቅርቦት ችግሩ እንዲፈታ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም መፍትሄ ማግኘት እንዳልቻሉ የገለጹት ደግሞ የከተማው ነዋሪ አቶ ቢረሳው አናጋው ናቸው። የወንበርማ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ባንቴ ታደሰ በበኩላቸው "የሽንዲ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ ጥያቄን መመለስ ባለመቻሉ ከህዝቡ ጋር በልማት ዙሪያ ተቀራርቦ መነጋገር አልተቻለም" ብለዋል። ከአሥር ዓመት በፊት በከተማው 10 ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ የተገነባው የውሃ ተቋም በአሁኑ ወቅት በሦስት እጥፍ ላደገው የነዋሪዎች ቁጥር ባለመብቃቱ ችግሩ መከሰቱን ገልጸዋል። በውሃ እጥረት ምክንያት በግንባታ ሥራ የተደራጁ ወጣቶች በቀን ከ500 እስከ 600 ብር በላይ ለውሃ በማውጣታቸው ምክንያት ሥራቸውን ለጊዜው ማቋረጣቸውን ተናግረዋል። የውሃ አቅርቦቱ ችግር እንዲፈታ ለክልሉ ውሃ ቢሮ በተደጋጋሚ የማሳወቅ ሥራ ሲሰሩ ቢቆዩም አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት በኩል ክፍተት መኖሩን አመለክተዋል። የክልሉ ውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ይመር ሃብቴ በበኩላቸው በከተሞች ያለውን የውሃ እጥረት ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በ60 ከተሞች በተለያየ የግንባታ ደረጃ ላይ የሚገኙ የውሃ ተቋማት እንዳሉ ጠቁመው፣ ከእዚህ በተጨማሪ እስከዛሬ ውሃ ያላገኙ ከተሞችን በመለየት የዲዛይንና የጥናት ሥራ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። የሽንዲ ከተማ ውሃ አቅርቦት እጥረትን ለመፍታት የአንድ ውሃ ተቋም የዲዛይንና የጥናት ሥራ ተጠናቆ በ70 ሚሊዮን ብር በጀት ተግብራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩንም አስታውቀዋል። የውሃ ተቋሙ ግንባታ በሚቀጥለው ዓመት መጨረሻ ድረስ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ የሽንዲ ከተማንና በዙሪያው ያሉ 40 ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ አንደሚጠበቅ ተናግረዋል። የሚገነባው የውሃ ተቋም ከ10 እስክ 20 ዓመት የሚያገለግል ሲሆን ወጪውም ሙሉ ለሙሉ በክልሉ መንግስት እንደሚሸፈን ተናግረዋል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
465
በትምህርት ቤቶች የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ስነ ጤና አገልግሎት ማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ይፋ ሆነ ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤት የንጹህ መጠጥ ውሃ እና የስነ ጤና አገልግሎት ማስፈጸሚያ ስትራቴጂክ ይፋ አደረገ። በትምህርት ሚኒስቴር እና በዎተር ኤይድ ኢትዮጵያ የቴክኒክና የፋይናንስ ድጋፍ የተዘጋጀውን ሰነድ እስከ 2020 ድረስ ለአምስት ዓመት የሚቆይ ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ሊራዘም እንደሚችል ተገልጿል። በአሁኑ ወቅትም በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ በደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች፣ በሶማሌና አፋር ክልሎች በተመረጡ 382 ወረዳዎች በሚገኙ ከ800 በላይ ትምህርት ቤቶች ስራው ተጀምሯል። ስትራቴጂውን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስፈልገውን ወጭ በተመለከተ ላቀረብንላቸው ጥያቄ "ገንዘቡ ከተለያዩ ባለርሻ አካላት የሚገኝና ድጋፍ በሚደረግላቸው ትምህርት ቤቶች ያለው ግብዓት የተለያየ ስለሚሆን በትክክል ማስቀመጥ አይቻልም" የሚል ምላሽ ሰጥተውናል። በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሃመድ አህመዲን እንዳሉት፤ በአገሪቷ በመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና የስነ ጤና አገልግሎት ውስንነት ይስተዋላል። በንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት፣ ንጽህናው የተጠበቀ መጸዳጃ ቤት ባለመኖር ለተለያዩ በሽታዎች ተጋልጠው ከትምህርት ገበታቸው የሚፈናቀሉና በትምህርታቸው ደካማ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ብዙ ናቸው ብለዋል። በኢትዮጵያ 40 በመቶ የመጀመሪያ እና 63 በመቶ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ብቻ የንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት አላቸው። የተሻሻለ የመጸዳጃ ቤት ያላቸው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 32 በመቶ እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህረት ቤቶች 47 በመቶ ብቻ መሆናቸውንም ገልጸዋል። ከዎተር ኤይድ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር እየተተገበረ ያለው "የትምህርት ቤት ንጹህ መጠጥ ውሃ፣ ንጽህናና ስነ ጤና ስትራቴጂ ሰነድ" የአገሪቷን ትምህርት ቤቶች የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን መቶ በመቶ ለማድረስ ያግዛል ብለዋል። በስነ ጤና በኩልም በትምህርት ቤቶች መጸዳጃ ቤቶችና የአካባቢ ንጽህና ወደ 80 በመቶ ከፍ በማድረግ የተማሪዎችን መጠነ ማቋረጥ እንቀንሳለን ብለዋል። ለዚህ ስኬታማነት የክልል ትምህርት ቢሮዎች፣ የትምህርት ባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች በቅንጅት መስራት ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት። የዎተር ኤይድ ኢትዮጵያ ዳይሬክተር ወይዘሮ ቤቴልሄም መንግስቱ፤ በአማራ፣ ኦሮሚያና ትግራይ ክልሎች በተመረጡ ትምህርት ቤቶች የንጹህ መጠጥ ውሃ የማቅረብና ለተማሪዎች የሚመጥኑ መጸዳጃ ቤቶች የመገንባት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በትምህርት ዘርፍ እደርስባቸዋለሁ ያላቸውን የዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ያስቀመጣቸውን ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ለመደገፍ አንሰራለን ብለዋል። በዚህም ከትምህርት ገበታ የሚፈናቀሉ ተማሪዎችን ቁጥር ለመቀነስና የንጽህና ጉድለት በትምህረት ጥራት ላይ የሚያደርሰውን ተጽዕኖ ለመቀነስ አስፈላጊውን የገንዘብና የሙያ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። እንደ አስፈላጊነቱ የሚራዘመው የአምስት ዓመት "የትምህርት ቤት ንጹህ መጠጥ ውሃ፣ ንጽህና እና ስነ ጤና ስትራቴጂ ሰነድ" የተዘጋጀው በዎተር ኤይድ ኢትዮጵያ የገንዘብ ወጪ መሆኑንም ገልጸዋል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
466
በውሀ እጥረት ተቸግረናል— የአሶሳ፣የአርባምንጭና የጭሮ ከተሞች ነዋሪዎች በአካባቢያቸው ባጋጠማቸው የንፁህ መጠጥ ውሀ እጥረት መቸገራቸውን የአሶሳ፣ የአርባ ምንጭና በጭሮ ከተሞች አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነዋሪዎች ገለጹ። በአሶሳ ከተማ በተለምዶ ገብርኤል በሚባለው አካባቢ ነዋሪ ወይዘሮ ደስታ ጃራ እንዳሉት የቧንቧ ውሃ አገልግሎት ከተቋረጠ ሁለት ወራት ሆኖታል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ በቦቴ እያከፋፈለ ያለው ውሀ ስለማይዳረስ ከሌላ አካባቢ ለሚቀዱት አንድ የባለ 25 ሊትር ጀሪካን ውሀ አምስት ብር እየከፈሉ ለመጠቀም መገደዳቸውንና እንግልት መዳረጋቸውን ተናግረዋል ። በከተማው የመናኸሪያ አካባቢ ነዋሪ አቶ ትዕዛዙ ደንድር በበኩላቸው የውሃ እጥረቱ የተከሰተው ከጥር ወር ጀምሮ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ” የቧንቧ ውሃ በሳምንት አንዴ ቢመጣም በበቂ ሁኔታ ሳንቀዳ ተመልሶ ስለሚጠፋ ተቸግረናል”ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ ውሃና ፍሳሽ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሃሩን መንሱር ስለጉዳዩ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ በከተማው የውሃ አቅርቦት በቂ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ” ከአምስት ዓመታት በፊት የከተማውን 20 ሺህ ነዋሪ ታሳቢ በማድረግ የተሰራው የውሀ ማስፋፋፊ ፕሮጀክት አሁን ላይ አገልግሎት እየሰጠ ቢሆንም የነዋሪው ቁጥር በእጥፍ በማደጉ እጥረቱ ተፈጥሯል ” ብለዋል ። በተያዘው ዓመት አጋማሽ ላይ ሁለት የውሃ ጉርጓዶች መድረቃቸውና ሌሎች ጉርጓዶች የሚያመርቱት ውሃ መቀነሱ ደግሞ እጥረቱን እንዳባባሰው አመልክተዋል፡፡ “ጽህፈት ቤቱ ችግሩን በጊዜያዊነት ለመፍታት የውሃ ስርጭቱን በፈረቃ በማከፋፈል ላይ ነው “ያሉት ስራ አስኪያጁ ስርጭቱ በማይዳረስባቸው አካባቢዎች በቦቴ ለማዳረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የተጀመሩ የሁለት ጥልቅ ጉድጓዶች ቁፋሮ ስራ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የስድስት ጥልቅ የውሃ ጉርጓዶች ጥናት እየተካሄደ እንደሚገኝና በቀጣይ ዓመት እስከ ህዳር ወር ድረስ ግንባታውን ለመጀመር እየተዘጋጁ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል። በተመሳሳይ የውሃ እጥረት ከተከሰተ ከሁለት ወር በላይ በመሆኑ መቸገራቸውን የገለጹት ደግሞ በአርባ ምንጭ ከተማ ሼቻ ክፍለ ከተማ ቤሬ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ደርብ ገሠሠ ናቸው፡፡ እሳቸው እንዳመለከቱት ከዚህ ቀደም በሣምንት ሶስት ጊዜ ይመጣ የነበረው የቧንቧ ውሀ አሁን ላይ በ15 ቀን አንድ ጊዜ ብቻ መምጣት ጀምሯል ። ውሀ ከሌላ አካባቢ ለማምጣት ለትራንስፖርት ጨምሮ ከፍተኛ ወጭ እያወጡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል ። በክፍለ ከተማው የጫሞ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ በላይነሽ ዓባይ በበኩላቸው ውሃ ፍለጋ ሰፊ ጊዜ እያባከኑ የዕለት ተዕለት ሥራቸውን በአግባቡ እያከናወኑ አለመሆናቸውን ተናግረዋል ። በአካባቢየቸው በሳምንት ሁለት ጊዜ ይመጣ የነበረው የቧንቧ ውሀ ለሁለት ወር ያክል በመቋረጡ ከፍተኛ ወጭ በማውጣት ከሌላ አካባቢ ለመቅዳት መገደዳቸውን የተናገሩት ደግሞ በነጭ ሣር ክፍለ ከተማ የዕድገት በር ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ቤቲ ታምሩ ናቸው፡፡ የአርባ ምንጭ ከተማ ውሃና ፊሳሽ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ አብርሃም ላለፉት ሁለት ወራት ያጋጠመው የውሃ እጥረት ከኃይል አቅርቦት እጥረት ጋር የተያያዘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አገልግሎት የሚሰጡ ሶሰት የውሃ ፓምፖች ቢኖሩም ባጋጠመ የኤሌክትሪክ ኃይል መቀነስ እየሰራ ያለው አንዱ ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል ። ” ችግሩን ለመፍታት ከኤሌክትሪክ አገልግሎት አርባ ምንጭ ዲስትሪክት ጋር እየተነጋገርን ነው” ብለዋል ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአርባምንጭ ዲስትሪክት አገልግሎት መስጫ ማዕከል ኃላፊ አቶ ገረመው ወንድምሁነኝ በበኩላቸው በዚህ ሳምንት የመስመር ለውጥ የሚደረግ በመሆኑ ችግሩ እንደሚፈታ አስታውቀዋል ። ይህ በእንዲህ እንዳለ በጭሮ ከተማ የኮንዶሚኒየም ሰፈር ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ ኤልሳቤጥ ለገሰ የውሃ አቅርቦት እንደተቋረጠባቸውና ለችግር መዳረጋቸውንም ነው የተናገሩት። በአካባቢያቸው የውሀ ስርጭት ከተቋረጠ 11 ቀናት እንደሆነም ጠቁመዋል። ወይዘሮ አይናለም አበራ በበኩላቸው ንጹህ የመጠጥ ውሃ በመጥፋቱ ምግብ ለማብሰልም ሆነ የልጆቻቸውን ንፅህና ጠብቀው ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ መቸገራቸውን ገልጸዋል። ለመጠጥ የሚሆን የታሸገ ውሀ ለመግዛት በመገደዳቸው በገቢያቸው ላይ ጫና እንዳሳደረባቸውም ጠቅሰዋል ። ” ችግሩ እንዲፈታ በተደጋጋሚ የሚመለከተውን አካል ብናሳውቅም ያገኘነው መፍትሔ የለም”ያሉት ደግሞ ወይዘሮ አበራሽ ዘመድኩን ናቸው፡፡ የጭሮ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ ጉልላት አማረ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ ለከተማውና አካባቢው አገልግሎት ከሚሰጡ ሁለት የጥልቅ ውሀ ጉድግዶች የአንዱ የውሀ መሳቢያ ፓምፕ በቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በመቃጠሉ ችግሩ መከሰቱን ተናግረዋል ። ” እጥረቱን በጊዜያዊነት ለመፍታት ውሀ በፈረቃ እያሰራጨን ነው” ያሉት አቶ ጉልላት የተቃጠለውን ፓምፕ የሚተካ ማሽን ከክልል እያስመጡ መሆኑንና ችግሩም አምስት ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ይፈታል ብለዋል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
467
ለህብረተሰቡ የሚቀርበው ንፁህ የመጠጥ ውሃ በአገር አቀፍ የጥራት መለኪያ መስፈርት ውስጥ ማለፍ አለበት ተባለ በውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አማካኝነት ለህብረተሰቡ የሚቀርበው ንፁህ የመጠጥ ውሃ በኢትዮጵያ ተስማሚነትና ምዘና መስፈርት ውስጥ ማለፍ እንዳለበት የኢትዮጵያ ውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢትዮጵያ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ፌዴሬሽን ከውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው “የአገር አቀፍ የከተሞች የመጠጥ ውሃ ዘርፍ የውሃ ጥራት ሰርተፍኬትና እውቅና መርሃ ግብር ” በዛሬው እለት አዲስ አበባ ውስጥ ተካሄዷል። በውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ፍሬነሽ መኩሪያ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ለህብረተሰቡ የሚቀርበው ውሃ ጥራት በኢትዮጵያ ተስማሚነትና ምዘና ድርጅት አማካኝነት መረጋገጥ እንዳለበት የታመነ በመሆኑ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ሥራ ተጀምሯል። የምዘናው መስፈርቶች እስከ ሃምሳ የሚደርሱ ሲሆኑ ከአላስፈላጊ ኬሚካሎች ጋር የተያያዙና በሰው ጤናና ህይወት ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ተህዋሲያን ነፃ መሆኑን መሰረት ያደረጉ ናቸው። በስነ-ስርዓቱ ላይ የደሴ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ፅህፈት ቤት የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰጥቶታል። ፅህፈት ቤቱ አውቅናውን ያገኘው የሚያቀርበው ውሃ ጥራት በኢትዮጵያ ተስማሚነትና ምዘና ድርጅት አንዲመዘን በራሱ ተነሳሽነት ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ነው። ፅህፈት ቤቱ የጥራት ማረጋገጫ ሲያገኝ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑም ተመልክቷል። በመላ አገሪቷ 55 ከተሞች የንጹህ መጠጥና ፍሳሽ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የውሃ ሃብታቸውን ከማስተዳደርና በተደራሽነት ላይ ከመስራት ባለፈ የሚያቀርቡትን ውሃ ጥራት የማረጋገጥና እውቅና የማግኘት አሰራር ሂደት ውስጥ እስከ መጪው ነሃሴ 2010 ዓ.ም ባለው ጊዜ መግባት እንዳለባቸውም ሚኒስትር ዲኤታዋ አሳስበዋል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የተሳተፉ የክልል የውሃና ፍሳሽ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች በበኩላቸው በሚቀጥሉት አራት ወራት ውስጥ ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልተው ወደ አሰራሩ እንደሚገቡ ገልፀዋል። የሃዋሳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ፅህፈት ቤት ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ጌታቸው ፀሃዩ ከተማዋ የላብራቶሪ እቃዎችንና ባለሙያዎችን አሟልቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከደሴ ከተማ ተሞክሮ በመውሰድ በሚቀጥሉት ወራት አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት ምዘናውን ለማከናወን ዝግጅት ይደረጋል ብለዋል። በተለይም ቀጣይነት ባለው መልኩ የውሃ ጥራትን የተመለከቱ ዳታዎችን ከማደራጀት፣ ከመከታተልና አሰራርን ከማዘመን ረገድ ጠቃሚ ልምድ መውሰዳቸውንም ገልፀዋል። የድሬዳዋ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሃመድ ሙርሲ በበኩላቸው አስካሁን ወደ አሰራሩ ያልገባነው ትልቅ ትኩረት የሰጠነው በተደራሽነት ላይ ስለሆነና በገለልተኛ ተቋም ጥራቱን ለማረጋገጥ ትኩረት ስላልሰጠን ነው ሲሉ ተናግረዋል። እስከ ነሃሴ 30 ቀን 2010ዓ.ም ድረስ በከተማው ሊፈቱ የሚችሉ ክፍተቶችን በመለየትና በመፍታት ወደ አሰራሩ እንገባለን ያሉት ስራ አስኪያጁ ከአካባቢው ውሃ ጫዋማነት ጋር የተያያዘው ችግር ግን እስከ 1 ቢሊዮን ብር የሚጠይቅና ጊዜ የሚፈልግ ነው ብለዋል። በዚህም መሰረት ከተማው በአቅሙ ሊሰራቸው የሚችለውንና ለጤና ጉዳት የሚያመጡ ችግሮችን ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው ብለዋል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
468
የዳዋ ጨፋ ወረዳ ነዋሪዎች ለንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር መጋለጣቸውን ገለጹ 427 Share ደሴ ጥቅምት 4 / 2012 በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በዳዋ ጨፋ ወረዳ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተመደበላቸው የውሃ ፕሮጀክቶች ባለመጠናቀቃቸው ለንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር መጋለጣቸውን ነዋሪዎች ገለጹ። ፕሮጀክቱ በያዝነው ዓመት እንደሚጠናቀቁ የወረዳው ውሃና ኢነርጂ ልማት ጽህፈት ቤት አስታውቋል። የወረዳው አንዳንድ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደተናገሩት በወረዳው ላለፉት አራት ዓመታት የተጀመረው ፕሮጀክት እስካሁን ባለመጠናቀቁ ንጽህና የተጠበቀ ውሃ ለማግኘት አልቻሉም። በአንድ ዓመት ይጠናቀቃል የተባለው ፕሮጀክት ባለመጠናቀቁ ከውሃ እጥረትና ከውሃ ወለድ በሽታዎች ችግሮች አለመለቀቃቸውን አስተያየት ሰጪዎቹ አስረድተዋል። የዶዶ ቀበሌ ነዋሪ አቶ መሐመድ ከድር የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት የተጀመረው ፕሮጀክት ባለመጠናቀቁ ሴቶች ውሃ ለመቅዳት ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን እንደሚያባክኑ ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ”በየዓመቱ ‘ዘንድሮ ይጠናቀቃል’ እየተባለ ለፖለቲካ ፍጆታ ውሏል” ያሉት አስተያየት ሰጪው፣ ችግራቸውን ለማቃለል በክረምት ወቅት አጠራቅመው የሚጠቀሙት የዝናብ ውሃ ለውሃ ወለድ በሽታ እያጋለጠን ነው ብለዋል፡፡ በአካባቢያቸው ወንዝም ሆነ ምንጭ አለመኖሩ ችግሩን እንዳባባሰው ገልጸው፣ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥና በሕዝብ ላይ የሚቀልዱ አመራሮችና ግለሰቦችን ተጠያቂ እንዲያደርግም ጠይቀዋል፡፡ የቢላቻ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ሐዲያ ጀማል ከሁለት ሰዓት በላይ ተጉዘው የሚያገኙት ንጽህናው ያልተጠበቀ የወንዝ ውሃ በጤንነታቸው ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም ወረፋ ለመያዝ “ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ጀምሮ ስለምንጓዝ ጉልበታችንና ጊዜያችንን ከማጥፋታችን በተጨማሪ ሴቶች በመሆናችን ለጠለፋና ለመደፈር እየተጋለጥን በመሆኑ የሚመለከተው አካል ትኩረት ሊሰጥ ይገባል” ብለዋል፡፡ የዳዋ ጨፋ ወረዳ ውሃና ኢነርጂ ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ ተስፋዬ ተጠይቀው ፕሮጀክቱ በዲዛይን፣ተፈጥሯዊ አቀማመጥ፣ በመንገድ ችግርና በጀት ባለመለቀቁ መዘግየቱን አስታውቀዋል። ግንባታው በአማካይ 94 ነጥብ 5 በመቶ የደረሰው ፕሮጀክት በያዝነው ዓመት ማጠናቀቅ ለአገልግሎት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። ፕሮጀከቱ ከ20 ሺህ በላይ ሕዝብ ተጠቃሚ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅና ከ500 ሜትር ኩብ በላይ ውሃ የሚጠራቅምባቸው ታንከሮች እንደሚገነቡለት ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ በወረዳው ያለውን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋን አሁን ካለበት ከ68 ወደ 78 በመቶ እንደሚያደርሰውም አስረድተዋል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
469
የንፁህ መጠጥ ዉኃ ችግር እና ቅድመ መከላከል የጤና ፖሊሲ ደካማነት ተከትሎ የ’አተት’ በሽታ ወረርሽኝ በድጋሚ ተከሠተ .. (ይድነቃቸው ከበደ) አጣዳፊ ተቅማጥ እና ተውከት በምህፃሩ ‘አተት’ ተብሎ የሚጠራው በሽታ በፍጥነት የመሠራጨት ፀባይ ያለው እና በጊዜው አስቸኳይ ሕክምና ካላገኘ ብዙዎችን ለሞት የሚዳርግ አደገኛ የወረርሽኝ በሽታ ነው ።በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የሚከሰተው ይህ የወረርሽኝ በሽታ አብዛኛው መንስኤ የንፁህ መጠጥ ዉኃ ችግር ሲሆን ፣ የአካባቢ እና የግል ንጽህና ችግር በዋነኛነት የወረርሽኙ መንስኤ ነው። በኢትዮጵያ የ’አተት’ ወረርሽኝ የመጀመሪያው እና ትልቁ መፍትሔ ወረርሽኙ እንዳይከሰት የቅድመ መከላከል ‘ የማህበረሠብ ተኮር የጤና ፖሊሲ’ ትልቅ ሚና እንዳለው በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች ይመክራሉ። ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የወረርሽኙ መከሰት ተከትሉ፤ የንፁህ መጠጥ ዉኃ ችግር እና የማህበረሠብ ተኮር የጤና ፖሊሲ ደካማነት እንደሆነ በብዙዎች ዘንድ ይታመናል። በዚህም መክንያት በተደጋጋሚ የሚከሰተው የ’አተት’ በሽታ ቁጥር ቀላል የማይባል የሰውን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን አብዛኛውን ሰው ለከፍተኛ ህመም ዳርጎል። በአሁን ወቅት በኢትዮጵያ በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል የተቀሰቀሰው የ’አተት’ ወረርሽኝ በሽታ ወደ ተቀረው አካባቢ፣ አዲስ አበባን ጨምሮ ሊዛመት እንደሚችል ሥጋት ያለ ሲሆን፤ ‘የአተት/ በሽታን’ አስመልክቶ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እየተሰጠ ያለው መግለጫ ግን በተቃራኒው ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ የህወሃት/የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የጤና ጥበቃ ሚኒስተር ሆነ በሚያገለግሉበት ወቅት ‘የአተት/ ‘በሽታ’ በተደጋጋሚ የተቀሰቀሰ ሲሆን ለብዙዎች ህመም እና የተወሰነ ሰዎች ለሞት ተዳርገዋል ። እኚህ ባለሥልጣን ለዓለም የጤና ጥበቃ ድርጅት ዳይሬክተርነት በሚወዳደሩበት ወቅት፤ የምረጡኝ ዘመቻ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲያካሂዱ “የወረርሽኝ እና ተላላፊ በሽታ” በታዳጊ ሃገራት ለማስቀረት እና ለመከላከል እንደሚሰሩ ጭምር ገልፆው ሲሆን፣ በተለይ በኢትዮጵያ “ቅድመ መከላከያ የጤና ፖሊሲ” ተግባራዊ በማድረግ የተስቦ እና የወረርሽኝ በሽታ መቆጣጠር እንደተቻለ እና ይሄን ልምድና ተሞኩሮ በዓለም ለመተግበር እንደሚሰሩ ቃል ገብተው እንደነበረ የሚታወሰ ነው።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
470
የውሃ እና የኃይል እጥረት ተጽዕኖ በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቶች እጥረት በማሕበረሰቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ እና በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳርፏል። This video file cannot be played. (Error Code: 102630) አውዲዮውን ያዳምጡ። 11:18 የንጹህ መጠጥ ውሃ እና የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት በኢትዮጵያ በተለይም የገጠሩ የአገሪቱ ክፍል70 ከመቶ አካባቢ የሚሆነው ሕዝብ ይኸውም ከ 10 ሰው ሰባቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ አለመሆናቸውን ጥናቶች ይጠቁማሉ :: ይህን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍ በተለይም ለመሰረታዊ ፍጆታም ይሁን ለምጣኔ ኃብት ዕድገት ወሳኝ የሆኑትን የኤሌክትሪክ ኃይል እና ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አገልግሎቱን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለመላው ሕብረተሰብ ለማዳረስ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ፈርጀ ብዙ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን መንግሥት እየገለጸ ነው :: ይሁን እንጂ በርካታ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ሌሎችም የኃይል አማራጮች ተሰርተው ከአገር አልፈው እንደ ኬንያ ታንዛንያ ጅቡቲ ሱዳን ፣ ርዋንዳ እና ሌሎችም ጎረቤት የአፍሪቃ አገራት ጭምር ከአገልግሎቱ ተጠቃሚ በማድረግ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ አስገኛለሁ የሚሉት የአገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለሥልጣን መሥሪያ ቤትም ሆነ የውሃ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር እንኳንስ የገጠሩን የአገሪቱ ክፍል ይቅርና የከተማውንም ሕብረተሰብ የኤሌክትሪክም ሆነ ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቶች በተገቢው መንገድ ማዳረስ እንደተሳናቸው ነው ሕብረተሰቡ በተደጋጋሚ ቅሬታውን የሚገልጸው :: የኤሌክትሪክ ኃይል በተደጋጋሚ መቋረጥ እና የፈረቃ አገልግሎት በአንዳንድ ከተሞችም ለዓመታት ያለ ኃይል አቅርቦት የኤሌክትሪክ መስመሮች በየመንገዱ ተዘርግተው የሚታዩበት ሁኔታ ተቋማቱን በመልካም አስተዳደር እጦት ሲያስወቅሱት መቆየታቸውን የመስኩ ባለሙያዎች ይገልጻሉ :: እንዲህ ዓይነቱ ውስብስብ ችግር ባልተቀረፈበት ሁኔታ መንግሥት የአገልግሎት ክፍያ የታሪፍ ማሻሻያ ጥናት ማቅረቡ በማሕበረሰቡ ዘንድ ቅሬታን እንደፈጠረ ይነገራል :: በኢትዮጵያ በአዲሱ ታሪፍ አስፈላጊነት እና በኤሌክትሪክ እና ንጹሕ የመጠጥ ውሃ ማሻሻያ ስራዎች ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጡን አቶ ብዙነህ ቶልቻን በውሃ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ጠይቀናቸው ነበር :: Symbolbild Idee Strom Glühbirne (colourbox/K. T. Segundo ) « በኢትዮጵያ አልፎ አልፎ የ ኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ የሚታይባቸው ሁኔታዎች አሉ :: ይህም በተጠቃሚው ሕብረተሰብ ላይ እንደዚሁም የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎች ላይ ተጽዕኖ የሚፈጥርበት ሁኔታ መኖሩ እሙን ነው :: የኃይል መቆራረጥ እጥረት ችግርን ለመፍታት የማሰራጫ መስመሮችን የማሻሻል ሥራዎች በተለያዩ ከተሞች እየተሰሩ ይገኛሉ :: አንዳንዶቹም ወደመጠያቀቁ ተቃርበዋል :: በአዲስ አበባ በባህር ዳር በመቀሌ በደሴ በድሬዳዋ በጅማ በአዳማ እና በአዋሳ የ8 ከተሞችን የሥርጭት የማከፋፈያ ኔትወርክን የማሻሻል የሙከራ ሥራ እየተሰራ ነው :: በስድስት ተጨማሪ ከተሞችም ማለትም በጎንደር አዲግራት ሻሸመኔ ወላይታ ሶዶ ሐረር እና ደብረማርቆስም የማሻሻያ ሥራ ለመስራት ሚኒስቴር መስሪያቤቱ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል ::» በኢትዮጵያ ያጋጠመውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና የመቆራረጥ ችግር ለማቃለል በ 14 ከተሞች እንዲሁም በአዲስ አበባ አንድ ሶስተኛ ያህሉ አካባቢ መንግሥት የጀመራቸው የኤሌክትሪክ ማሻሻያ ሥራዎች እየተጠናቀቁ መሆናቸው ታውቋል :: የአየር ንብረት ሲለዋወጥ የሚጠፋውንም የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ አማራጭ ዘዴዎች መቀየሳቸውን አቶ ብዙነህ ገልጸውልናል:: « በአሁኑ ወቅት የንጹህ መጠጥ እጥረትን ለማቃለል በ342 ወረዳዎች በ 24 መካከለኛ ከተሞች እና በ 120 አነስተኛ ከተሞች ላይ የንጹህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት የማስፋፋት ሥራ በፕሮግራም ተቀርጾ እየተሰራ ነው :: በዚህም እንቅስቃሴ ከስድስት ሚልዮን የሚልቁ ዜጎችን የንጹሕ መጠጥ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ::» የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዋና ዋልታ እና ምሰሶ ይሆናል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የታላቁ የህዳሴ ግድብ የግንባታ እንቅስቃሴም የተለያዩ እክሎች እንደገጠሙት እየተነገረ ነው :: በመንግሥት በጀት እና በሕዝብ ሃብት የግንባታው ሥራ የተጀመረው ይህ ግድብ አሁን በሚታየው የአሰራር ፍጥነቱ በቀጣዮቹ 10 ዓመታትም የመጠናቀቁ ነገር አሳሳቢ መሆኑን በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ሥጋታቸውን ይፋ አድርገው ነበር :: ግንባታው በመከላከያ ብረታብረት እና ኢንጂነሪንግ / ሚቴክ / አቅም ብቻ ከግብ ሊደርስ እንደማይችልም ተጠቁሟል : : በጣሊያኑ ተቋራጭ ሳሊኒ የሚካሄደው የግድቡ የሲቭል ኢንጂነሪንግ ክፍል ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ ሲገኝ በሚቴክ የሚከናወነው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ ክፍሉ ማለትም የጄኔሬተር እና ተርባይኖች ተከላ ስራው ግን መጓተቱን የውሃ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ባለፈው ሰሞን ይፋ አድርጓል :: ከዓመታት በፊት መንግሥት በነደፈው የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የሃገሪቱን የምጣኔ ሃብት ዕድገት ለማሳለጥ ይሰራሉ እየተባሉ ዘሬም የግንባታ ሥራቸው የተጓተቱ አያሌ ፕሮጀግቶች በተለይም በኃይሉ ዘርፍ ከባድ የኢኮኖሚ ማነቆ መፍጠራቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምሕር የሆኑት ዶክተር ታደለ ፈረደ ያስረዳሉ:: Äthiopien Grand Renaissance Staudamm (Reuters/T. Negeri) «በመጀመሪያ የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በመንግሥት የተጀመሩ በርካታ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክት ዕቅዶች ነበሩ :: ይሁን እና ሁሉም በሚባል ደረጃ አልተጠናቀቁም :: በተለይም በኃይል ሥርጭቱ ዙሪያ ግንባታን ማስፋፋት ብቻ ሳይሆን አቅርቦቱን በተገቢው መንገድ ማሻሻል ተገቢ ነው :: የኢነርጂው ዘርፍ አገሪቱ ለነደፈችው የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ስኬት እንዲሁም ለኢንዱስትሪው ክፍለ ኢኮኖሚ ዋንኛ ግብአት በመሆኑ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ነው ::አሁን ያሉት ኢንዱስትሪዎች ከውሃ በሚገኝ የሃይል ምንጭ የሚንቀሳቀሱ እንደመሆናቸው ኢንዱስትሪዎች በጥራት እና በብቃት አምርተው በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ በመሆን በሙሉ አቅም ለመስራት በቂ የኃይል አቅርቦት ያስፈልጋቸዋል :: የሃይል መቆራረጥ ከአቅማቸው በታች እንዳያመርቱ እና ማሽኖቻቸው እንዲበላሹ በማድረግ ለኪሳራ ይዳርጋቸዋል የስራ አጥ ቁጥርም እንዲበራከት ያደርጋል:: ይህ ችችግር በምጣኔው ሃብት ላይ ከባድ ተጽዕኖ ፈጥሯል ::» በስኳር እና የተለያዩ ፕሮጀክቶች የአፈጻጸም ችግር አሳይቷል በሚልዮን የሚቆጠር ከፍተኛ የበጀት ብክነትም እንዳለበት ተረጋግጧል ተብሎ በተደጋጋሚ በመንግሥት አካላት ሲወቀስ የነበረው ሚቴክ ለግድቡም ሥራ መዘግየት ምክንያት መሆኑ ይፋ ሆኗል :: በቅርቡ እንኳ ግድቡ ከሚያስፈልጉት 16 የ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ሁለቱ ብቻ ተተክለው ሙከራ ቢደረግም በቴክኒክ እክል አለመሳካቱ የግንባታውን ሥራ የበለጠ እንዲጓተት አድርጎታል ተብሏል :: በኮንትራት ውሎቹ ላይ ከ አራት ዓመታት በፊት ሁለት ጄኔሬተሮችን በያዝነው ዓመት ደግሞ ቀሪዎቹን በሙሉ የመትከል ሥምምነት ቢኖርም አስካሁን አንዱም ስራ አለመጀመሩን ነው ውስጥ አዋቂ ምንጮች የሚገልጹት:: የውሃ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህን እንደ ኃይል አቅርቦቱ ሁሉ ተመሳሳይ ችግር የሚታይበትን የንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረትስ ለመፍታት ምን እቅድ ተነድፏል ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ መልስ ሰተውናል :: « የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት የሚከሰትበት ሁኔታ እንዳለም ታውቋል:: በተለይም በደረቅ እና ከፊል ደረቃማ አካባቢዎች አስተማማኝ እና ዘላቂነት ያለው የንጹሕ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ማቅረብ ማዳረስ የሚቻልበት መርሃ ግብር ተነድፎ ከዚህ ዓመት ጀምሮ ወደ ተግባር የሚገባበት ሂደት ተጀምሯል :: እ.ኤ.አ በ 2011 ዓ.ም በጀት ዓመት ውስጥ ዕቅዱን መተግበር የሚጀመርበት ሁኔታ አለ :: በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ውስጥ እስካሁን ከ6 ሚልዮን በላይ ዜጎችን የንጹሕ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ::» ለበርካታ የአፍሪቃ ሃገራት የኤሌክትሪክ ኃይል አምርቶ የመሸጥ እቅድ ያለው የኢትዮጵያ መንግሥት በሃገር ውስጥ የሚታየውን እጥረት ለመቅረፍ እሳካሁን የተጓዘበት መንገድ የሕብረተሰቡን ችግር ሙሉ በሙሉ መፍታት አልቻለም:: ያም ቢሆን መንግሥት የሃይል እጥረትን ለመቅረፍ ከጎርጎሪዮሳዊው 2010 - 2017 ዓ.ም የሚዘልቅ " ብርሃን ለሁሉም " የተሰኘ መርሃ-ግብር ነድፎ የጀመረው እንቅስቃሴ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል በቀጣዮቹ ዓመታት የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ያስችላል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል:: የንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማቃለልም በአነስተኛ ወንዞች ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የሚችል ቴክኖሎጂን በመተግበር እና ከፀሃይ ብርሃን ተጨማሪ ሃይል በማመንጨት አገልግሎቱን ለብዙሃኑ ተደራሽ ለማድረግ የተግባር ሥራ መጀመሩ ታውቋል :: ይሁንና በተለይም የኃይሉ ዘርፍ መሰረታዊ መፍትሄ ባላገኘበት ሁኔታ የውሃ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር አዲስ የታሪፍ ማሻሻያ ለውይይት ማቅረቡ በሕብረተሰቡ ዘንድ ቅሬታ መፍጠሩ አልቀረም :: የሚኒስቴሩ ሕዝብ ግንኙነት እና ኮምኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ስለዚሁ የሚሉት አለ :: « የታሪፍ ማስተካከያ የቀረበበት ዋናው ምክንያት ከዛሬ 12 ዓመታት በፊት ማለትም እ.ኤ.አ በ1998 ዓ.ም የተደረገውን የታሪፍ ለውጥ ማሻሻል በማስፈለጉ ነው :: የኃይል አቅርቦት ገቢ እና ወጭን ለማመጣጠን እንዲሁም የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥን ችግር ለመቅረፍ ተጨማሪ የፋይናንስ ወጭ በመጠየቁ ነው :: ይህንንም ፋይናንስ ለአገልግሎት ከሚቀርበው የኤሌክትሪክ ሽያጭ በተቻለ መጠን በተመጣጣኝ እና አስተማማኝ በሆነ ሁኔታ ገቢ መሰብሰብ የሚቻልበት መንገድን ታሳቢ ያደረገ ነው :: ማሻሻያው በሚኒስትሮች ምክርቤት ከመጽደቁ በፊት ጥናት እና ውይይት ላይ ሲሆን ዝቅተኛ ገቢ ያለው የሕብረተሰብ ክፍል ላይ ተጽዕኖ አይፈጥርም ::ከዚህ ሌላ ከ 50 kw/hr በታች ተጠቃሚ የሚሆኑ ደንበኞች ላይ ምንም ዓይነት ጭማሪ አይኖርም ::» የኤሌክትሪክ ኃይሉን ሥርጭት እጥረት ለመቅረፍ በየቦታው መንግሥት የጀመራቸው ፕሮጀክቶች አብዛኛዎቹ ዛሬም ድረስ ከግንባታ እስከ ጥራት ዘርፈ ብዙ ችግሮች እንዳለባቸው የመስኩ ባለሙያዎች ይገልጻሉ:: በቅርቡ እንኳ 50 ሜጋ ዋት ለማመንጨት የኮንትራት ስምምነት የተፈረመበት የረጲ የደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ከግማሽ በታች 25 ሜጋ ዋት ብቻ ማመንጨቱ ብዙዎችን ማነጋገሩ አልቀረም :: የኢኮኖሚክስ ባለሙያው ዶክተር ታደለ ፈረደ በኢትዮጵያ የሚታየው የኤሌክትሪክ ኃይል ሥርጭት እጥረት እና ተደጋጋሚ መቋረጥ በኢንዱስትሪው ክፍለ-ኢኮኖሚም ሆነ በማሕበረሰቡ የዕለት ተዕለ ኑሮ ላይ መጠነሰፊ ችግር እያስከተለ መሆኑን ይገልጻሉ :: አሁን በኢትዮጵያ የሚታየውን የኃይል እጥረት ለማቃለል የግሉን ኢንቨሥትመንት በዘርፉ እንዲሳተፍ ማድረግ አንዱ መፍትሄ ሊሆን እንደሚችልም ዶክተር ታደለ ይመክራሉ:: « መንግሥት የኃይል ማምረቱንም የሥርጭቱንም አገልግሎት አጠቃሎ በሞኖፖል መያዙ ለሃይል እጥረቱ ዋና ምክንያት እንደሆነ ይታመናል :: በዚህም ምክንያት ያለውን የተመረተውን እንኳን በበቂ ሁኔታ ማሰራጨት እና ማዳረስ አልተቻለም :: አዲሱ የመንግሥት አስተዳደር በቅርብ እንደ ኢነርጂ ሴክተሩ ያሉትን ዘርፎች በተወሰነ ደረጃ ወደ ግል ለማዞር የነደፈው ዕቅድ የሚደገፍ ነው :: ከሌሎች ሃገራት ተሞክሮ አንጻር የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ቢያንስ ኃይል የማከፋፈሉ ስራ ላይ ቢሳተፍ አሁን የሚታየውን የኢነርጂ አቅርቦት ችግር መቅረፍ ይቻላል :: »
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
471
‹‹ውኃ ላይ ተቀምጠን ውኃ መጠማት የለብንም፡፡›› ዶክተር ማማሩ አያሌዉ ባሕር ዳር፡ ሕዳር 27/2012ዓ.ም (አብመድ) ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደርና አካባቢዋ የንፁሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ችግር በተደጋጋሚ ይነሳል፡፡ ይህንን ችግር ለመፍታት ያስችላል የተባለ ውይይት ዛሬ በባሕር ዳር ሲካሄድ ውሏል፡፡ በውይይቱም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡ የባሕር ዳር ከተማ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘላለም አስፋዉ ‹‹በዘርፉ የሚገኙ ተቋማት በቅንጅት ያለመሥራት ችግር የከተማዋን ሕዝብ በቂ ውኃ እንዳያገኝ አድርገውታል›› ብለዋል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ችግር፣ የውኃ መስመሮች በሕገ-ወጥ ግለሰቦች በተደጋጋሚ መቆረጥ፣ ትልልቅ ተቋማትና ኩባንያዎች የሚጠቀሙት የውኃ መጠን ከፍተኛ መሆንና በሚጠቀሙት ልክ ያለመክፈል ችግሮች መኖራቸው በውይይቱ ተነስቷል፡፡ የሕዝብ ቁጥር መጨመር፣ ለሚሠራጨዉ ውኃ የሚጠየቀዉ ክፍያ ከተለያዩ ከተሞች ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ መሆን እንዲሁም የግብዓት ችግሮች የውኃ ስርጭቱን ዝቅተኛና ፍትሐዊ እንዳይሆን እንዳደረጉት ነው ምክትል ሥራ አስኪያጁ የገለጹት፡፡ የከተማዋ የእድገት መሪ ዕቅድ (ፕላን) ሲሠራ የመሠረተ ልማት ተግባራትን ታሳቢ ያላደረ መሆን፣ ለውኃ አገልግሎቱ በቂ በጀት አለመመደብና ሌሎችም የችግሩ መንስሔዎች ከተሳታፊዎች በውይይቱ ተነስተዋል፡፡ የክልሉ ውኃ መስኖና ኢነርጅ ልማት ቢሮ ኃላፊ ማማሩ አያሌው (ዶክተር) ከተማዋ ላይ እያጋጠመ ያለውን የውኃ ችግር ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ለመፍታት ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ከአውስኮድና ከአማራ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ጥናት ስለመደረጉ ተናግረዋል፡፡ ችግሩን ለመፍታትም በአጭር፣ በመካከለኛና በረዥም ጊዜ የሚከናወኑ ተግባራት ስለመኖራቸውም ዶክተር ማማሩ ገልጸዋል፡፡ በጥናቱ መሠረትም በጃፓን መንግሥት ድጋፍ በአምስት ሚሊዮን ብር ዳግማዊ ቴዎድሮስ ክፍለ ከተማ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ይጀምራል፤ ከ12 እስከ 18 ወራት የሚወስድ የመስመር ዝርጋታ ደግሞ በአውስኮድ እንደሚከናወን አስታውቀዋል፡፡ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት በዚህ ወቅት 52 ከመቶ ብቻ ነው፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
472
የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግራቸው በመፈታቱ መደሰታቸውን የአንኮበር ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ 1178 Share ደብረ በርሃን ግንቦት 21/2010 የነበረባቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በመፈታቱ መደሰታቸውን በሰሜን ሸዋ ዞን አንኮበር ወረዳ ነዋሪዎች ገለፁ። የወረዳው ውሃና ኢነርጅ ጽህፈት ቤት በበኩሉ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ሁለት የውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን አስታውቋል፡፡ በአንኮበር ወረዳ የደረፎ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አራጋው ፈንታ በሰጡት አስተያየት ቀደም ሲል በአካባቢያቸው ውሃ ባለመኖሩ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለማግኘት በቀን ከሁለት እስከ ሦስት ሰዓት በእግር ይጓዙ ነበር፡፡ አሁን ከአጎራባች ቀበሌ ተስቦ በየቤታቸው በገባላቸው ቧንቧ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ በመሆናቸው ለዘመናት ያቀርቡት የነበረው ችግር እንደተፈታላቸው ገልፀዋል፡፡ የእዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ አሰለፈች በየነ በበኩላቸው በአካባቢያቸው በነበረው የውሃ እጦት በተለይ እንስሳት የሚጠጡትን ውሃ ፍለጋ ከረዥም ርቀት ለማምጣት ስለሚከብዳቸው እንስሳቱ በሦስት ቀን አንድ ጊዜ ብቻ ይጠጡ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በየቤታቸው የቧንቧ ውሃ ተጠቃሚ ከመሆናቸው ባለፈ የከብት ማጠጫና የልብስ ማጠቢያ ገንዳ ተሰርቶ ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ የአይገብር ቀበሌ ነዋሪ አቶ ተክለመድን ሳህለ በበኩላቸው ቀበሌው የአፋር ጠረፋማ አካባቢ ተጎራባች በመሆኑ በአካባቢያቸው የውሃ አማራጭ አለመኖሩን ጠቁመዋል። ረዥም ርቀት ተጉዘው በግመል ለሰውና ለእንስሳት ውሃ ለመቅዳት ሲሉ ጊዜና ጉልበት ከማባከን ባለፈ በወረፋ ጥበቃ ከሰዎች ጋር ለግጭት ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመንግስት፣ መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና በሕብረተሰቡ ተሳትፎ በተገነባው የውሃ ታንከር ችግራቸው ተፈቶ እንስሳት ጭምር ያለችግር ውሃ በማግኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የአንኮበር ወረዳ ውሃና ኢነርጅ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በለጠ ጌጡ በበኩላቸው በአካባቢው ይስተዋል የነበረው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት የመልካም አስተዳደር ችግር ፈጥሮ መቆየቱን ተናግረዋል። ችግሩን ከግምት ውስጥ በማስገባትም በተሰራው ስራ በአሁኑ ወቅት በ12 ሚሊዮን 486 ሺህ ብር የተገነቡ ሁለት የውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን አስረድተዋል። ” የውሃ ተቋማቱ 15 ሺህ 700 ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሲሆን ከ20 ዓመት በላይ አገልግሎት መስጠት ይችላሉ ” ብለዋል። ከአንኮበር ወረዳ በ11 እና 8 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ያሉ ምንጮችን በማጎልበት በየቤቱ የንጹህ ውሃ ተጠቃሚ ከማድረግ በላፈ 7 የከብት ማጠጫና 5 የልብስ ማጠቢያ ገንዳዎች መሰራታቸውን ጠቁመዋል፡፡ አቶ በለጠ እንዳሉት ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቁት ሁለቱ የውሃ ታንከሮች 120 ሜትር ኪዩብ ውሃ የመያዝ አቅም አላቸው፡፡ የውሃ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው አገልግሎት መጀመር የወረዳውን የገጠር ንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን አምና ከነበረበት 64 በመቶ ወደ 71 በመቶ ከፍ እንዲል ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ “የሰሜን ሽዋ ዞን ውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ኤፍሬም ምንሽር በበኩላቸው በተያዘው ዓመት የገጠር ንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋኑን ለማሳደግ ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች 33 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ተመድቦ እየተሰራ ነው” ብለዋል። እነደኃላፊው ገለጻ፣ በአሁኑ ወቅት 23 የውሃ ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደት ላይ ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥም 6ቱ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፤ ቀሪዎቹም በተለያየ ደረጃ በግንባታ ላይ መሆናቸውን ነው የገለጹት። በዞኑ ቀደም ሲል የተገነቡ 531 አነስተኛ የገጠር ንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ይገኛሉ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
473
የእነዋሪ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ችግር እስከ ጥር እንደሚቀረፍ ተገለጸ፡፡ ባሕር ዳር፡ ታኅሳስ 07/2012ዓ.ም (አብመድ) የእነዋሪ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ እታገኝ ገለታዉ ከሰፈራቸው ርቀው ውኃ ስለሚቀዱ ክፉኛ መቸገራቸውን ለአብመድ ገልጸዋል፡፡ ወይዘሮ እታገኝ እንዳሉት ከ15 ቀን አንድ ጊዜ ብቻ ነው ውኃ እያገኙ ያሉት። ለወይዘሮ እታገኝና ለሌሎችም ሴቶች አንድ ብር በማስከፈል ውኃ ሲያስቀዱ አግኝተን ያነጋገርናቸው አቶ ዘነበ ቅጣዉ ለሕዝቡ በወረፋ የሚያከፋፍሏት አነስተኛ ውኃ ‹‹ወፌ›› እየተባለ ከሚጠራ አንድ ብቸኛ ምንጭ የሚገኝ ነው፡፡ ተጨማሪ የውኃ አቅርቦት ባለመኖሩ ሕዝቡ እየተቸገረ ነው፡፡ የሞረትና ጅሩ ወረዳ ውኃና ኢነርጂ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደረጀ አለማየሁ እንዳሉት የችግሩ መሠረታዊ መንስኤ ከ22 ዓመታት በፊት ይሰጥ የነበረው አገልግሎት ሳይቀየር ባለበት ሁኔታ መቀጠሉ ነው፡፡ የጽሕፈት ቤት ኃላፊው እንደተናገሩት መግፊያ ‹ፓምፕ›፣ ‹ዲናሞ› እና ‹ኬብል› በማርጀታቸዉ የዉኃ ግፊቱን አናሳ እንዲሆን አድርጎታል፤ የከተማዉ ነዋሪ ቁጥርም ከፍተኛ እድገት በማሳየቱ የሕዝቡን የንጹህ መጠጥ ውኃ ፍላጎት ባለው አሰራር ማሟላት አልተቻለም፡፡ ብልሽቶች ሲከሰቱም ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የባለሙያ የቅንነት ችግር መኖሩ ችግሩን እንዳባባሰው ነው አቶ ደረጀ አለማየሁ የገለጹት፡፡ ‹‹ለችግሮቹ መፍትሔ ለመስጠትም በፈረቃ የውኃ አገልግሎቱ እንዲደርስ እያደረግን ነዉ፤ ኦዲተርን ጨምሮ ለሙያዉ ተገቢውን ባለሙያ በመቅጠርና አሠራር ላይ ያሉ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ በማድረግ መፍትሔ እየተሰጠ ነው፤ ጊዜ ሳያባክኑ በባለቤትነት እንዲንቀሳቀሱ የተሻለ አመለካከት ያላቸው ባለሙያዎችንም መድበናል›› ብለዋል፡፡ ፓምፕ፣ ዲናሞና ኬብል ለመግዛት በወረዳዉ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በጀት መያዙንም ተናግረዋል፤ ግዢዉም በሂደት ላይ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ ‹‹ሥራዉ ተጠናቅቆ ጥር ወር የተሻለ አገልግሎት ይኖራል ብለን እንጠብቃለን›› ብለዋል ኃላፊው። በክልሉ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተሠራ ያለ ‹ኘሮጀክት›' መኖሩን የጠቀሱት ኃላፊው የኘሮጀክቱ የመጀመሪያ የግንባታ ምዕራፍ 86 ከመቶ፤ ሁለተኛ ምዕራፍ ደግሞ 52 ከመቶ መድረሱን ገልጸዋል። ከተቋራጩ በተገኘ መረጃ መሠረት አድርገው ምዕራፍ ሁለት በተያዘው ዓመት የካቲት ወር እንደሚጠናቀቅ አስታውቀዋል። በዘላቂነት ግን በሰከንድ 5 ነጥብ 5 ሊትር የሆነውን የውኃ አቅርቦት ወደ 22 ነጥብ 5 ሊትር ከፍ ለማድረግ በእቅድ መያዙን ከወረዳው ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
474
በባሕር ዳር ከተማ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጭ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ግንባታ ነገ ይጀመራል፡፡ ባሕር ዳር፡ መስከረም 7/2012 ዓ.ም (አብመድ) ከ525 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሚደረግበት የባሕር ዳር ከተማ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ግንባታ ሥራ ነገ እንደሚጀመር ተገለጸ፡፡ አዲስ የሚጀመረው የንጹሕ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቱ የባሕር ዳር ከተማን የውኃ አቅርቦት ችግር በከፊል ያሻሽላል ተብሏል፡፡ ፕሮጀክቱ ከ525 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚፈጅም ታውቋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሙሉ ወጪ ከጃፓን መንግሥት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚሸፈንም ነው የተገለጸው፡፡ የባሕር ዳር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ይርጋ ዓለሙ ለአብመድ እንደተናገሩት የንጹሕ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቱ የሚገነባው በባሕር ዳር ዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ ክፍለ ከተማ ነው፡፡ የግንባታ ሥራው ነገ ተጀምሮ በሁለት ዓመታት እንደሚጠናቀቅም አቶ ይርጋ አስታውቀዋል፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅም የባሕር ዳር ከተማን የንጹሕ መጠጥ ውኃ ችግር በከፊል ያሻሽላል ብለዋል፡፡ በባሕር ዳር ከተማ ያለው የንጹሕ መጠጥ ውኃ ሽፋን 60 በመቶ ነው፤ ይህም ከክልሉ ሽፋን አማካይ ያነሰ ነው፡፡ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከክፍለ ከተማው የሚተርፍ ውኃ ከተገኘ ከተማ አስተዳደሩ በራሱ በጀት ለመሥራት ጥረት ያደርጋል ብለዋል ሥራ አስኪያጁ፡፡ ይህ ፕሮጀክት በመንግሥት ጥረት የተገኘ መሆኑን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ በተያዘው በጀት ዓመት ክልሉ በሚበጅተው 120 ሚሊዮን ብር ተጨማሪ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ለመሥራት መታሰቡንም ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
475
በምዕራብ ጎንደር ዞን ከ30 ሺህ በላይ ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሆኑ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገጠራማ አካባቢዎች ዘንድሮ በተገነቡ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ከ30 ሺህ በላይ ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን የዞኑ የግብርና ልማት መምሪያ አስታወቀ። ተጠቃሚዎች በበኩላቸው የውሃ ተቋማት በአቅራቢያቸው በመገንባቱ ጊዜና ጉልበታቸውን እንደቆጠበላቸው ተናገሩ። በመምሪያው የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ዋና የሥራ ሂደት መሪ አቶ ካሳ አሰጌ ለኢዜአ እንደገለጹት በገጠራማ አካካቢዎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋንን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው። በተያዘው በጀት ዓመት ከ30ሺህ በላይ ዜጎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ተጠቀሚ ማድረግ የተቻለው 20 የእጅ ጉድጓድና ሦስት የጥልቅ ጉድጓድ ውሃ ፕሮጅክቶች ተገንብተው በመጠናቀቃቸው መሆኑንም ገልጸዋል። በገጠር ከተገነቡት የውሃ ፕሮጅክቶች በተጨማሪ በመተማ ወረዳ ኮኪት ከተማ ተጨማሪ የውሃ ተቋም እንዲገነባ መደረጉን አቶ ካሳ ተናግረዋል፡፡ የውሃ ተቋማቱን ለመገንባት ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች 34 ሚሊዮን ብር ድጋፍ መደረጉንና ሕብረተሰቡም በገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበት ካደረገው አስተዋጽኦ በተጨማሪ ከ300 ሺህ ብር በላይ ማዋጣቱን ተናግረዋል። እንደ አቶ ካሳ ገለጻ፣ በአሁኑ ወቅትም 30 የእጅ ጉድጓዶችና አራት የጥልቅ ጉድጓድ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል የእጅ ጉድጓዶቹ እስከ ነሀሴ ወር አጋማሽ ድረስ ተጠናቀው ለአገልግሎት ይበቃሉ። የጥልቅ ጉድጓድ ፕሮጀክቶቹም በቀጣዩ ዓመት መጀመሪያ ሩብ ዓመት ይጠናቀቃሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው አቶ ካሳ ያስታወቁት። “ተጠናቀው ለአገልግሎት የበቁት የውሃ ፕሮጀክቶች የዞኑን የውሃ ሽፋን ከ70 ወደ 74 በመቶ ማሳደግ የቻሉ ሲሆን ቀሪዎቹ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁም ሽፋኑ ወደ 81 በመቶ ከፍይላል” ብለዋል። በዞኑ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል በመተማ ወረዳ ላስታ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ገብሩ ጥሩነህ እንዳሉት ቀደም ሲል የመጠጥ ውሃ በአህያ ጭኖ ለማምጣት ከ3 እስከ 4 ሰዓት ለመጓዝ ይገደዱ እንደነበር አስታውሰዋል። በእዚህም ንጽህናው ያልተጠበቀ የወንዝ ውሃ በመጠቀም ለተለያዩ የውሃ ወለድ በሽታዎች ሲጋለጡ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት የውሃ ተቋማቱ መገንባታቸው ይህን ችግራቸውን ይፈታል የሚል አምነት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ሌላው የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ አለምሰገድ ሽፈራው በበኩላቸው የመጠጥ ውሃ ከወንዝ ለማስቀዳት ልጃቸውን ከትምህርት ቤት የሚያስቀሩበት አጋጣሚ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት በአቅራቢያቸው የውሃ ተቋም መገንባቱ ንጽህናው የተጠበቀ ውሃ እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ ልጃቸው ትምህርቱን በአግባቡ ለመከታተል እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። በኮኪት ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ ሰናይት አማረ በበኩላቸው በከተማዋ የጋራ ቦኖ ውሃ ተጠቃሚ እንደነበሩ ጠቁመው፣አሁን ከጥልቅ ጉድጓዱ ቤታቸው ድረስ ቧንቧ በመግባቱ ለወረፋ ጥበቃ ያባክኑት የነበረው ጊዜ መቆጠቡን ገልጸዋል። በእዚሁ ከተማ የሚኖሩት አቶ ቢሰጥ አድኖ በበኩላቸው በቤታቸው የንጹህ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸው እንዳስደሰታቸውና ለውጡ ለከተማዋ እድገት አንድ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
476
የጊምቢ ከተማ ነዋሪዎች በንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት መቸገራቸውን ገለፁ 1028 Share ጊምቢ አምሌ 5/2010 በንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት መቸገራቸውን የጊምቢ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ፡፡ የነዋሪዎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር ለማቃለል ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን የኦሮሚያ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ አስታውቋል፡፡ ቅሬታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል የቀበሌ 04 ነዋሪ አቶ በንቲ ደበላ እንደገለፁት በከተማው በተከሰተው የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት ምክንያት አገልግሎቱን የሚያገኙት በሳምንት አንድና ሁለት ቀን ብቻ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ንጽህናውን ያልጠበቀ ወራጅ ውሃ ለመጠጥነት በመጠቀም እሳቸውን ጨምሮ ቤተሰባቸው ለጤና ችግር መጋለጣቸውን ገልፀዋል፡፡ የቀበሌ 01 ነዋሪ ወይዘሮ ማርታ ዩሐንስ በበኩላቸው በከተማው ”በተከሰተው የንፁህ መጠጥ ውኃ ችግር በሳምንት በምናገኘው አነስተኛ የንፁህ መጠጥ ውሃ የልጆቻቸውን ንፅህና ለመጠበቅ፣ የቤት ውስጥ ስራን ለመስራትና ንፁህ ውሀ ለመጠጣት አልቻልንም” ብለዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ቤተሰባቸው ለውሀ ወለድ በሽታ መጋለጣቸውን ተናግረዋል ። ችግሩን አስመልክቶ ለሚመለከተው አካል ቢያሳውቁም እስካሁን ምላሽ እንዳላገኙ አስታውቀዋል፡፡ በ02 ቀበሌ የሆቴል ባለቤት ወይዘሮ ኢዲሴ ደለቴራ በበኩላቸው “የንፁህ መጠጥ ውሀ እጥረቱ ለደምበኞቻችንና ተገልጋዩች ተገቢውን አገልግሎት እንዳንሰጥ እንቅፋት ሆኖብናል” ብለዋል። የከተማው ውሀ አቅርቦትና ፍሳሽ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ ጉዲና ኮሉ ስለጉዳዩ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ ችግሩ የተከሰተው ነባሩ የውሃ ኘሮጀከት አቅርቦት ከፍላጎት ጋር ባለመመጣጠኑ ነው፡፡ ከ15 ዓመት በፊት ለ15 ሺህ ነዋሪዎች አገልግሎት እንዲሰጥ የተገነባው የውሃ ኘሮጀክት አሁን ላለው ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪ ማዳረስ ባለመቻሉ የተከሰተ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ችግሩን ለመፍታት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በመደበው በጀት ጌሌል ወንዝ ላይ በ2002 ዓ. ም. የካቲት ወር የተጀመረው ፕሮጄክት በሶስት ዓመታት ተጠናቆ ስራ እንደሚጀምር ተስፋ ቢደረግበትም ከታሰበው በላይ መጓተቱን ገልፀዋል። የኦሮሚያ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ገዘኻኝ ለሜቻ በበኩላቸው በ2002 የተጀመረው የከተማው የንፁህ መጠጥ ውሃ ኘሮጀክት በ2005 መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም ለአምስት ዓመት መጓተቱን ገልፀዋል፡፡ “የውሃ ማስተላለፊያ ቱቦዎቹን ዝርጋታ ለማከናወን የከተማው መሬት አቀማመጥ አመቺ አለመሆን፣ ከተዘረጋ በኋላ በየቦታው በሚያጋጥም የመሬት መንሸራተትና ውሃውን የሚገፉ ፓምፖች በየጊዜው መበላሸታቸው ለፕሮጄክቱ ግንባታ መጓተት መንስኤ ነው” ብለዋል። “ቱቦዎቹን ጨምሮ በተደጋጋሚ በሚበላሹት ፓምፖችና የፕሮጄክቱ ዲዛይን ዙሪያ እየተደረገ ያለው ጥናት በሚቀጥለው ሳምንት ስለሚጠናቀቅ ችግሩን ተረድተን ለረዥም አመታት የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ የቆየውን ይህንኑ የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት ለመቅረፍ የመፍትሄ ሐሳብ እናገኛለን” ብለዋል። በጌሌል ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ የሚገኘው ይኸው የንፁህ መጠጥ ውሀ ፕሮጄክት ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚጨርስ የገለጸው የቢሮው ምክትል ኃላፊ እስከ አሁን ከ162 ሚሊዮን ብር በላይ እንደፈጀ ለማወቅ ተችሏል። ስራ ሲጀምርም በቀን ከሶስት ሺ ሜትር ኪዩብ በላይ ውሀ በማምረት እስከ 120ሺ የሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች ለሚቀጥሉት 30 ዓመታት አስተማማኝ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በዚሁ ጊዜ ተገልጿል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
477
ሁለት ቢሊዮን ሰዎችን ንጹሕ የመጠጥ ውሃ እጥረት ማጋጠሙ የሚያሳፍር ነው ተባለ። ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገሮች የሚኖሩ ሴቶች ውሃን ለማግኘት ብለው በአማካይ የሰላሳ ደቂቃ መንገድ በእግር እንደሚጓዙ የገለጸው የድርጅቱ ሪፖርት ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገሮች የሚኖሩ ሕዝቦች፣ ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን እና የመጸዳጃ አገልግሎትን የማያገኙ ከሆነ ለተለያዩ በሽታዎች እንደሚጋለጡ፣ ለተመጣጣኝ ምግብ እጥረት፣ ለትምህርት ዕድል ማነስ እና ለሥራ እጦት የሚጋለጡ መሆናቸውን አስታውቋል። የዚህ ዝግጅት አቅራቢ ዮሐንስ መኰንን - ቫቲካን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በጎርጎሮሳዊው 2019 ዓ. ም. የውሃ አቅርቦትን በማስመልከት ባቀረበው ዓመታዊ ሪፖርቱ በዓለማችን ውስጥ ሁለት ቢሊዮን ሰዎች ንጹሕ የመጠጥ ውሃን እንደማያገኙ አስታወቀ። ከ2002 ዓ. ም. ጀምሮ ንጹሕ የመጠጥ ውሃን ማግኘት ከሰብዓዊ መብቶች መካከል አንዱ ሆኖ መጽደቁን ያስታወቀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት በዓለማችን ለሁለት ቢሊዮን አንድ መቶ ሚሊዮን ሰዎች ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እንደሚጎድል፣ አራት ቢሊዮን ሰዎች ደግሞ ጥራቱን እና ደህንነቱን የጠበቀ የመጸዳጃ አገልግልት እንደሌላቸው ገልጿል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዘላቂ ልማትን ለማምጣት በዘረጋው እቅዱ እስከ 2022 ዓ. ም. ድረስ ለዓለም ሕዝብ በሙሉ ንጹሕ የመጠጥ ውሃን እና ጥራቱን የጠበቀ የመጸዳጃ አገልግሎትን ለማዳረስ እቅድ እንዳለው አስታውቋል። የውሃ አቅርቦትን ማሳካት ረጅም ጊዜን ይጠይቃል፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በድርጅቱ ከታቀፈው ከትምህርት፣ ሳይንስ እና ባሕል ጽሕፈት ቤት (ዩኔስኮ) ጋር ሆነው ባዘጋጁት የጎርጎሮሳዊው 2019 ዓ. ም. ሪፖርት እንዳስታወቁት ለዓለማችን ሕዝብ በቂ የውሃ አቅርቦትን ተግባራዊ ለማደረግ ረጅም ጊዜን እንደሚጠይቅ ገልጸው ይህን እቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ላይ የሚገኙ 32 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፕሮጀክቶች፣ እንደዚሁም 41 ሌሎች ዓለም አቀፍ የግል ድርጅቶች መኖራቸው አስታውቀዋል። ሰብዓዊ ክብርን ማስጠበቅ አስፈላጊ የመብት ጉዳይ ነው፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባሕል ጽሕፈት ቤት ዋና ጸሐፊ የሆኑት ወይዘሮ ኦድሪይ አዙሌይ እንደገለጹት ለዓለማችን ሕዝብ ንጹሕ የመጠጥ ውሃን እና ጥራቱን የጠበቀ የመጸዳጃ አገልግሎትን ለማዳረስ ከተፈለገ የዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ የጋራ ተነሳሽነት እንደሚያስፈልግ አስረድተው እስካሁን በሕብረቱ ያልታቀፉ መንግሥታት መኖራቸው ለእቅዱ ተግባራዊነት እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል ብለዋል። የአካባቢ ጥበቃ መጓደል የውሃ ልማትን አደጋ ላይ ጥሎታል፣ በተባበሩት መንግሥታት የእርሻ ልማት ድርጅት (ኢፋድ) በኩል ስጋታቸውን የገለጹት የድርጅቱ ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ጂልበርት ሁንግቦ በበኩላቸው፣ የአካባቢ ጥበቃ መጓደል ጠቅላላውን የዓመት የውሃ ልማት ጥይስቄን ወደ 45 በመቶ ከፍ በማድረጉ የተነሳ ወደ 40 ከመቶ ዝቅ ያለው ዓመታዊ የዓለም የምርት መጠን እስከ ጎርጎሮሳዊው 2050 ዓ. ም. ድረስ ባሉት ዓመታት ውስጥ ዓለማችን አደጋ ውስጥ እንደሚወድቅ ያመለክታል ብለዋል። አንድ ሚሊዮን ከግማሽ የዓለማችን ሕዝብ ንጹሕ ያልሆነ ውሃን በመጠጣት ለጉዳት ተጋልጧል፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሪፖርቱ እንዳስታወቀው በዓለማችን አንድ ሚሊዮን አራት መቶ ሺህ ሰዎች ንጹሕ ያልሆነ ውሃን በመጠጣት ሊመጣ በሚችል በሽታ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ፣ ከእነዚህም መካከል አብዛኛዎቹ ሕጻናት መሆናቸውን ከመጋቢት 2 እስከ መጋቢት 6 ቀን 2011 ዓ. ም. በኬንያ ዋና ከተማ በናይሮቢ፣ የአካባቢ ጥበቃን አስመልክቶ በተደረገው ጉባኤ ላይ አስታውቋል። አደጋው በድህነት ሕይወት ውስጥ የሚገኙትን ያጠቃል፣ በቂ የሆነ ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት መጓደል በደሃ አገሮች የሚገኙ ሕዝቦችን እንደሚጎጋ፣ ከእነዚህም መካከል ሴቶችን፣ ሕጻናትን እና አዛውንትን፣ በይበልጥም የተፈናቀሉትን እንደሚጎዳ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት ገልጾ ንጹሕ የመጠጥ ውሃን የማግኘት መብት ከሌሎች ሰብዓዊ መብቶች ተነጥሎ እንደማይታይ ገልጿል። ሪፖርቱ አክሎም በከተሞች አካባቢ የሚገኙ ደሃ ቤተሰቦች ንጹሕ የመጠጥ ውሃን በውድ ዋጋ ገዝተው ለመጠቀም መገደዳቸውን ገልጿል። የአፍሪቃ ሴቶች ውሃን በአቅራቢያቸ አያገኙትም፣ ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገሮች ከሚኖር ሕዝብ መካከል ግማሹ ለጤና አስተማማኝ የሆነ ንጹሕ የመጠጥ ውሃን እንደማያገኝ ያስታወቀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት፣ በእነዚህ አገሮች ውስጥ ከሚገኙ ሕዝቦች መካከል 24 ከመቶ ብቻ ንጹሕ የመጠጥ ውሃን እንደሚያገኝ እና 28 ከመቶ የሚሆኑት የቤተሰብ ክፍሎች ደግሞ በጋራ የመጸዳጃ ቤት እንደሚገለገሉ አስታውቋል። ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገሮች የሚኖሩ ሴቶች ውሃን ለማግኘት ብለው በአማካይ የሰላሳ ደቂቃ መንገድ በእግር እንደሚጓዙ የገለጸው የድርጅቱ ሪፖርት ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገሮች የሚኖሩ ሕዝቦች፣ ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን እና የመጸዳጃ አገልግሎትን የማያገኙ ከሆነ ለተለያዩ በሽታዎች እንደሚጋለጡ፣ ለተመጣጣኝ ምግብ እጥረት፣ ለትምህርት ዕድል ማነስ እና ለሥራ እጦት የሚጋለጡ መሆናቸውን አስታውቋል። ጥገኝነት ጠያቂዎች እና ተፈናቃዮች የችግሩ ሰለባ ይሆናሉ፣ በትውልድ አገራቸው የሚፈናቀሉት እና የጥገኝነት ጠያቂዎች የሚገኙበት ሁኔታ ለንጹሕ የመጠጥ ውሃ እና ለመጸዳጃ አገልግሎት ምቹ እንዳልሆነ የተባበሩ መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት አስታውቆ በጎርጎሮሳዊው 2017 ዓ. ም. ወደ 70 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ከመኖሪያቸው እንዲፈናቀሉ መገደዳቸውን ገልጿል። በየዓመቱ በአማካይ ከ25 ሚሊዮን ሰዎች በላይ ደግሞ በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት እንደሚሰደዱ፣ ይህም ከሃምሳ ዓመታት በፊት ከሚሰደዱት የሰዎች ቁጥር ጋር ሲወዳደር በእጥፍ መጨመሩን ሪፖርቱ አስታውቋል። ውሃን ማግኘት በጦርነት ሆኗል፣ ከ1972 ዓ. ም. ወዲህ የውሃ ፍላጎት በየዓመት በአንድ ከመቶ እንደሚጨምር ያስታወቀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት የውሃ ፍላጎታቸውን ለማሟላት በአገሮች መካከል ጦርነቶች መካሄዳቸውንም ገልጿል። በዚህም መሠረት ውሃ ይገባኛል በሚል ሰበብ ከ1992 ዓ. ም. እስከ 2001 ዓ. ም. ድረስ ባሉት ዓመታት ውስጥ 94 ጦርነቶች መካሄዳቸውን፣ ከ2002 እስከ 2010 ዓ. ም. ድረስ 263 ጦርነቶች መካሄዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት ገልጾ ግጭቶቹ በሦስት እጥፍ ማደጋቸውን አስረድቷል። በውሃ እና በጤና አገልግሎቶች ላይ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ያስፈልጋል፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት በመጨረሻም በማደግ ላይ የሚገኙ አገሮች መዋዕለ ንዋያቸውን በውሃ እና በጤና አገልግሎት ተሻሽሎ ላይ ማፍሰስ እንደሚገባ ገልጿል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
478
የሀዋሳ ከተማን የመጠጥ ውሃ እጥረት ለማቃለል በ20 ሚሊዮን ብር እየተካሄደ ያለው የማስፋፊያ ፕሮጀክት ከ90 በመቶ በላይ ተጠናቀቀ አዲስአበባ፣ታህሳስ12 2003 (ሬዲዮፋና)የሀዋሳ ከተማን የመጠጥ ዉሃ እጥረት ለማቃለል በ20ሚሊዮን ብር እየተካሄደ ያለው የማስፋፊያ ፕሮጀክት ከ90 በመቶ በላይ መጠናቀቁን የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ ። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል የጥልቅ መጠጥ ዉሃ ግንባታ ለማከናወን የሚያስችል ጥናት መጠናቀቁም ተገልጧል ። የከተማዋ ከንቲባ አቶ ሽብቁ ማጋኔና ሌሎች የካቢኔ አባላት በወንዶ ገነት አካባቢ የሚገኘዉን የመጠጥ ዉሃ ማስፋፊያ ግንባታ ተዘዋዉረዉ ጎብኝተዋል ። ከንቲባዉ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት በሃዋሳ ከተማ የኢንቨስትመንት መስፋፋትን ተከትሎ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ የመጣዉን የመጠጥ ዉሃ ፍላጎት ለማርካት የተለያዩ ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸዉ ። ችግሩን ለማቃለል ከአለም ባንክ በተገኘ 16 ሚሊዮን ብር እና የከተማ አስተዳደር በመደበዉ የአራት ሚሊዮን ብር ወጪ የመጠጥ ዉሃ ፕሮጀክት ስራ ከ90 በመቶ በላይ መከናወኑን አስረድተዋል። ለከተማዋ ዘላቂ መፍትሄ ለማስገኘት ሃዌላ ወንዶና ጋራ ሊቀታ በተባሉ ስፍራዎች በሰከንድ ከ200 እስከ 300 ሊትር ዉሃ መስጠት የሚያስችሉ የሁለት ጥልቅ የዉሃ ጉድጓደችን ቆፋሮ ለማካሄድ የሚያስችል ጥናት መጠናቀቁን ገልጠዋል ። በጥናቱ መሰረት ፕሮጀክቱ ለሃያ አመታት ለከተማዋ አስተማማኝ የመጠጥ ዉሀ ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑም ተገልጧል ። የሃዋሳ ከተማ ዉሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ለጣ የታሞ በበኩላቸዉ በወንዶ ገነት አካባቢ በመገንባት ላይ ያለዉ የአምቦ የመጠጥ ዉሃ ፕሮጀክት በቅርቡ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በሰከንድ 55 ሊትር ማምረት እንደሚቻል ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ አማካሪ መሃንዲስ አቶ ታከለ ፍሰሃ በበኩላቸዉ በአሁኑ ወቅት የዋናዉ ምንጭ የማጎልበት ስራና የ10 ኪሎ ሜትር የዉሃ መስመር ዝርጋታ መጠናቀቁንና የአንድ ነጥብ ሶስት ኪሎ ሜትር መስመር ዝርጋታና ፣ አንድ ሚሊዮን ሊትር ዉሃ የሚይዝ የዉሃ ማጠራቀሚያ ጋን ግንባታ በመካሄድ ላይ መሆኑን ገልጠዋል።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
479
የንፁህ ውሃ ችግር ካለባቸው ሃገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ናት 1 year ago Kaliti Press የዓለም ውሃ ቀንን በማስመልከት የወጣ አዲስ ሪፖርት እንዳመለከተው ንፁህ የመጠጥ ውሃ የማያገኙ ሰዎች ቁጥር ወደ 844 ሚሊዮን ከፍ እንዳለ አመልክቷል። ዋተር ኤይድ የተባለው በጎ አድራጎት ድርጅትም የንፁህ ውሃ አቀርቦት ሳይኖር፤ ከጤና፣ ከትምህርትና ከፆታ እኩልነት ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ግቦችን ማሳካት ስለማይቻል ፖለቲከኞች ለውሃ አቅርቦት ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቀርቧል። በዓለም ዙሪያ ከሚገኙ ዘጠኝ ሰዎች መካከል አንዱ የንፁህ ውሃ አቅርቦት የለውም። ዋተር ኤይድ የተባለው የበጎ አድራጎት ድርጅት ይህንን እንዲል ያስቻለው፤ ሰዎች ምን ያህል ውሃን በቤታቸው ውስጥ ያገኛሉ ወይም ንፁህ ውሃን ለመቅዳት ከግማሽ ሰዓት በላይ በእግራቸው ለመጓዝ ይገደዳሉ የሚለውን በማጥናት ነው። ንፁህ ውሃን የማያገኙ ሰዎችን ብዛትን በተመለከተ አብዛኛውን ቁጥር የሚይዙት ቻይናዊያንና ሕንዳዊያን ናቸው። ነገር ግን ሃገሮች ካላቸው የህዝብ ቁጥር አንፃር በመቶኛ ሲሰላ የውሃ ችግር በተለይ በአፍሪካ የከፋ ነው። በንፁህ ውሃ አቅርቦት ችግር በቀዳሚነት የሚጠቀሱት ሃጋራትም ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ኡጋንዳ፣ ሶማሊያና የዲሞክራቲክ ኮንጎ ናቸው። ዋትር ኤይድ እንደሚለው 800 የሚደርሱ ከአምስት ዓመት በታች ዕድሜ ያላቸው ህፃናት ከንፁህ ውሃ እጦት ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባላቸውና ከተቅማጥ ጋር በተያያዙ ህመሞች በየዕለቱ ለሞት ይዳረጋሉ። የወደፊቱን የዓለም የንፁህ ውሃ አቅርቦትን ከማረጋገጥ የበለጠ አሳሳቢ ጉዳይ ስለሌለ መሪዎች ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው የበጎ አድራጎት ድርጅቱ አሳስቧል። የደቡብ አፍሪካ ከተማ የሆነችው ኬፕታውን ባለሥልታናት በቅርቡ እንዳስጠነቀቁት ዝናብ ካልዘነበ በመጪው ነሃሴ ወር ላይ በከተማዋ ያሉ የውሃ መስመሮች የውሃ አቅርቦታቸው ይቋረጣል። ከተማዋ የገጠማት የውሃ እጥረት በምድራችን ላይ ያለው የውሃ ሃብት ምንያህል ለአደጋ እንደተጋለጠ የሚያሳይ ነው ተብሏል።ነገር ግን ንፅህናው የተጠበቀ የውሃ አቅርቦትን የማያገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የምድራችን ነዋሪዎች የገጠማቸው ስጋት፤ የኬፕታውን ከተማ ከገጠማት ችግር በእጅጉ የከፋ እንደሆነ ተነግሯል። ቢቢሲ
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
480
የመቀሌን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረትን ለማቃለል 2 የውሃ ፕሮጀክቶች በተያዘው ዓመት አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ UNCATEGORIZED Last updated Sep 19, 2017 3,270 (ኤፍ.ቢ.ሲ)- የመቀሌ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረትን ለማቃለል ሁለት የውሃ ፕሮጀክቶች በተያዘው ዓመት አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ ተባለ። የመቀሌ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር መፍትሄ ሳያገኝ በመቆየቱ፥ በማህበረሰቡ የእለት ተእለት ኑሮ ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች በተለያዩ ጊዜያት ቅሬታቸውን ለፋና ብሮድካስቲንግ ሲያቀርቡ ነበር። የትግራይ ክልል ውሃ ሀብት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ተስፋሚካኤል ገብረዮሃንስ፥ የመቀሌ ከተማ የንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረትን የህብረተሰቡ እለታዊ ፍጆታ እና የአቅርቦት አለመመጣጠን ያስከተለው መሆኑን ይናገራሉ። የከተማዋ ዋና የውሃ ምንጭ ጥልቅ ጉድጓዶች ሲሆኑ፥ ጉድጓዶቹ ውሃ የማመንጨት አቅማቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተዳከመ መጥቷል። በአንጻሩ ደግሞ የከተማዋ የውሃ ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱ ችግሩ እንዲባባስ አድርጓል ሲሉም ዶክተር ተስፋሚካኤል ይናገራሉ። በአሁኑ ጊዜ ለተከማዋ ውሃ ከሚያቀርቡ የጥልቅ ጉድጓዶች ለከተማዋ ነዋሪዎች በአምስት ቀን አንድ ጊዜ ውሃ ለማቅረብ አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱን ሃላፊው ተናግረዋል። የከተማዋ የውሃ ችግር ዘላቂ መፍትሄ እስኪያገኝ ድረስ ያለውን ውሃ በፍትሃዊነት ለማዳረስ ጥረት እየተደረገ የቆየ ሲሆን፥ በ2010 ዓ.ም ግን ለበርካታ ዓመታት የዘለቀውን የውሃ እጥረት ማስቀረት የሚያስችሉ አዳዲስ ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል። ዶክተር ተስፋሚካኤል፥ ለመስኖ ልማት ፕሮጀክት ታስቦ የተገነባው እና 24 ሚሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የመያዝ አቅም ያለው “ገረብ ሰገን” ተብሎ የሚጠራው ግድብ በ2010 ዓ.ም የመጀመሪያ ወራት ላይ ለመጠጥ ውሃ አገልግሎት ይውላል ብለዋል። ከግድቡ ውሃውን ለህብረተሰቡ ለማድረስም የቧንቧ መስመር ዝርጋታው 94 በመቶ መጠናቀቁን ነው ሃላፊው የጠቆሙት። “ጭል ፈረስ” በተባለው አካባቢ የተቆፈሩ እና እያንዳንዳቸው በሰከንድ 50 ሜትር ኪዩብ ውሃ የማፍለቅ አቅም ያላቸው ሁለት ጥልቅ ጉድጓዶች ለመቀሌ ከተማ በቅርቡ ውሃ ማቅረብ ይጀምራሉ ነው የተባለው። በእነዚህ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ጊዜ ውሃ ለማግኘት ይጠበቅ የነበረውን የ5 ቀን ወረፋ ለማቅለል እንደሚረዱ ሃላፊው አስታውቀዋል። ወደ አገልግሎት ከሚገቡት ፕሮጀክቶች በተጨማሪ 300 ሜትር ኪዮቢክ ሜትር ውሃ የሚስጥ ፕሮጀክት፥ ግንባታ እንደሚጀመር የትግራይ ክልል ውሃ ሀብት ቢሮ አስታውቋል። የከተማዋን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት በዘላቂነት ለመፍታትም ከፌደራል መንግስት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ነው ቢሮው ያስተታወቀው።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
481
በአለማችን 2.1 ቢሊዮን ሰዎች ንጹህ ውሃ አያገኙም 35 በመቶ አፍሪካውያን የውሃ እጥረት ችግር ተጠቂ ናቸው በመላው አለም የሚገኙ 2.1 ቢሊዮን የተለያዩ አገራት ዜጎች አሁንም ድረስ ንጹህ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል፡፡ ተመድ ባለፈው ማክሰኞ ይፋ ባደረገው አለማቀፍ የውሃ ልማት ሪፖርት እንዳለው፤ በአለማችን 4 ቢሊዮን ያህል ሰዎች ለከፋ የውሃ እጥረት ተጋልጠው ይገኛሉ፡፡ የከፋ የውሃ እጥረት ያለባቸው አገራት አብዛኞቹ በአፍሪካ እንደሚገኙና በአህጉሪቱ ከ35 በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝብ የውሃ እጥረት ችግር ሰለባ እንደሆነ የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የአፍሪካ አገራት የህዝብ ቁጥር ከማደጉ ጋር በተያያዘ የውሃ ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ቢሆንም የውሃ አቅርቦትን ግን ለማሳደግ አለመቻሉን አመልክቷል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ቢዝነስ ኢንሳይደር እንደዘገበው፣ በአፍሪካ አጠቃላይ የውሃና የስነ-ንጽህና አቅርቦትን ለማሟላት 66 ቢሊዮን ዶላር ያህል ገንዘብ እንደሚስፈልግ ይገመታል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
482
በደብረ ማርቆስ ከተማ በንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ላይ የተደረገው ዋጋ ጭማሬ አግባብ አይደለም ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ገለፁ 3184 Share ደብረ ማርቆስ ሰኔ 14/2010 በደብረማርቆስ ከተማ ካለው የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት በተጨማሪ የዋጋ ጭማሬ መደረጉ አግባብ አይደለም ሲሉ የከተማው ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ገለፁ። አራት ብር የነበረው የአንድ ሜትር ኪዩብ ውሃ ወደ ሰባት ብር ከ50 ሳንቲም እንዲያድግ ተደርጓል። በከተማው የቀበሌ 06 ነዋሪ ወይዘሮ እጸገነት ይርዳው ለኢዜአ እንደገለፁት የከተማው የውሃ አቅርቦት ደካማ በመሆኑ ነዋሪውን እያማረረ ነው፡፡ ”ከዚህ ብሶ ደግሞ የዋጋ ጭማሪ መድረጉ ተገቢ አይደለም” ብለዋል። እሳቸው እንዳሉት ከዚህ በፊት ለውሃ በወር ከ30 እስከ 40 ብር ይከፍሉ እንደነበር አስታውሰው አጠቃቀማቸው ምንም ልዩነት ሳይኖረው አሁን በወር ከ200 ብር በላይ እንዲከፍሉ መጠየቃቸውን ገልፀዋል። አያይዘውም የውሃ ባለሙያዎቹ በየወሩ በትክክል ቆጣሪውን ስለማያነቡ የተደራረበ ሒሳብ በአንዴ በማምጣት ለመክፈልም ሲቸገሩ መቆየታቸው አስታውቀዋል። የቀበሌ 04 ነዋሪ ወይዘሮ ዘውዴ ተቀባው በበኩላቸው የውሃ ተመን መጨመር ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ በእለት ከእለት ኑሯቸው ላይ ተጽኖ እንደሚያሳድር ገልፀዋል፡፡ እሳቸው እንዳሉት ከዚህ በፊት ከ10 እስከ 15 ብር ይከፍሉ እንደነበር ጠቁመው፤ አሁን በተደረገው የዋጋ ማሻሻያ ከ60 ብር በላይ እንደከፍል ተደርጓል ሲሉ ቅሬታቸውን ተናግረዋል። ውሃ የሚያገኙት ደግሞ በሳምንት አንዴ በመሆኑ በዚሁ ወቅት በጀሪካን ሦስት ብር ድረስ ገዝተው እንደሚጠቀሙ ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም በከተማው የውሃ አቅርቦት ሳይሻሻል የዋጋ ጭማሪ መደረጉ ከቸርቻሪዎች የሚገዙበትን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር እንደሚያደርገው ጠቁመዋል። የቀበሌ 05 ነዋሪ አቶ ባየ ዝማሙ በበኩላቸው ”የውሃ ታሪፍ መጨመሩ የተጋነነና የኑሮ ውድነቱን ታሳቢ ያደረገ አይደለም” ብለዋል። እሳቸው የውሃ ስርጭቱ ከሳምንት በላይ ስለሚቆይ ውሃ ባለበት አካባቢ አካባቢ አንድ ጀሪካን እስከ ከ7 ብር በላይ እንደሚገዙ ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም የተደረገው የዋጋ ማስተካከያ አግባብ ባለመሆኑ መንግስት ያለውን ችግር ግምት ውስጥ በማስገባት መፍትሔ እንዲሰጥ ነዋሪዎች ጠይቀዋል። የከተማው ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ጌታነህ በሰጡት ምላሽ በክልሉ የውሃ አገልግሎት የዋጋ ተመን ከወጣላቸው መካከል ደብረማርቆስ አንዱ ነው ። ”አላማውም በከተማው ያለውን የውሃ እጥረት በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል ተጨማሪ ግንባታዎችን እና ነባሩን ፓምፕ ለመቀየር እንዲቻል ማህበረሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት በማሰብ ነው” ብለዋል ። በተጨማሪም የውሃ ተቋማቱ ጥገናና መሰል ጉዳዮች በሚያስፈልገው ወቅት እራሱን በራሱ ማስተዳደር እንዲቻል ታስቦ የዋጋ ጭማሬው መደረጉን አስረድተዋል። የውሃ ተመኑ ከዚህ በፊት ለአንድ ሜትር ኪዩብ 4 ብር ይከፈል እንደነበር አስታውሰው አሁን በተደረገው የዋጋ ማሻሻያ ወደ ሰባት ብር ከ50 ሳንቲም መተመኑን ገልፀዋል። በሚሰበሰበው ገቢም በወረፋ ለማዳረስ የሚደረገውን ጥረት ለማስቀረት የተለያየ የማስፋፊያ ስራ እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡ ”ነገር ግን ማህበረሰቡ የሚያቀርበው ቅሬታ ከዋጋ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ብቻ ሳይሆን ቀድመን ባለማሳወቃችን ጭምር በመሆኑ ለዚሁ ይርቅታ እንጠይቃለን” ብለዋል። በከተማ አስተዳደሩ ከ15 ሺህ 130 በላይ የውሃ ቆጣሪ መኖሩ ተጠቁሟል ።
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
483
የአክሱም ከተማ ነዋሪዎች በንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት መቸገራቸውን ገለፁ 1121 Share አክሱም ሀምሌ 28/2010 በአክሱም ከተማ በተከሰተው የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት መቸገራቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ፡፡ የከተማው ነዋሪ አቶ መብራቱ ወልደትንሳኤ እንዳሉት በከተማው በሚታየው የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር እየተዳረጉ ነው፡፡ የንፁህ መጠጥ ውሃ ለማግኘት ወደ ሌሎች አካባቢዎች በሚያደርጉት ጉዞም ለእንግልትና ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በጋራ እንዲጠቀሙበት በአካባቢያቸው የተሰራው የጋራ መጸዳጃ ቤትም በውሃ እጥረት ምክንያት አገልግሎት እየሰጠ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ የበጋሸት አብርሃ በበኩላቸው በከተማው ጥገና የሚያስፈልጋቸው የውሀ መስመሮች በወቅቱ ስለማይጠገኑ የሚለቀቀው ውሀ ህብረተሰቡ ጋር ሳይደርስ መንገድ ላይ እንደሚፈስ ገልጸዋል፡፡ በዚህም ምክንያንት ለህብረተሰቡ መድረስ የነበረበት ውሃ ለብክነት እየተዳረገ ነው፡፡ በተጨማሪም በአንዳንድ አካባቢዎች መስመር ቢዘረጋም ውሀ እንደማይደርሳቸው የገለፁት አቶ የበጋሸት መንግስት የነዋሪዎችን ጥያቄ በመገንዘብ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ ለከተማዋ እድገት የኮንስትራክሽን ስራ ወሳኝ መሆኑ እየታወቀ በውሃ እጥረት ምክንያት የግንባታ ስራ እያስተጓጎለ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የከተማው ነዋሪ አቶ በየነ ገብረማሪያም ናቸው፡፡ በመሆኑም መንግስት ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ የአክሱም ከተማ ከንቲባ አቶ ኤልያስ ካህሳይ በከተማዋ የንፁህ መጠጥ ውሀ ችግር መኖሩን አምነው ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እስኪገኝ ነዋሪዎች የሚያገኙትን ውሃ በቁጠባ እንዲጠቀሙ አስገንዝበዋል፡፡ የአክሱም ከተማ የውሃና ፍሳሽ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ብሩ በበኩላቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ ለከተማው ነዋሪ ለማዳረስ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በአቅርቦት እጥረት ምክንያት መስመር ተዘርግቶላቸው ውሃ የማይደርሳቸው አከባቢዎችን ችግር ለመቅረፍ ተጨማሪ ውሃ ለማምረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መስመሮችን ለመጠገንና አዳዲስ የውሃ ጉድጓድ ለመቆፈር ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን ሀላፊው ተናግረዋል፡፡ የጋራ መጸዳጃ ቤቶች አገልግሎት እንዲሰጡም የውሃ መስመር እንዲገባላቸው እየተሰራ በመሆኑ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ ገልጸዋል፡፡
[ 106 ]
[ "የንጹህ ውሃ መጠጥ" ]
[ "ስለ ንጽህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር, ግንባታ, የንጽህ መጠጥ ውሃ አገልግሎትን ተድራሽነት የሚያትቱ ሰነዶችን ጠቃሚወች ናቸው፡፡ ስለ ሌሎች መጠጥ አይነቶች ወይም ስለ ውሃ ብቻ የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች አይደሉም፡፡" ]
484
ምክር ቤቱ የጸረ-ሙስና ትግሉን የሚያጠናክሩ ሦስት ማሻሻያ አዋጆችን አጸደቀ , - ; .._2015_14. 0 257 168 ; 5; አዲስ አበባ ፤ጥር 62007 (ዋኢማ) - የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸረ-ሙስና ትግሉን የሚያጠናክሩ ሦስት የማሻሻያ አዋጆችን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ። - ; ምክር ቤቱ ትናንት  ባካሄደው 12ኛ መደበኛ ስብሰባው በህግ፣ ፍትህና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቀረቡትን የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ፣ የኮሚሽኑ ልዩ የስነ ስርዓትና የማስረጃ ህግ እንዲሁም የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የቀረቡትን የማሻሻያ አዋጆች በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። - ; የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ አቶ አህመድ አባጊሳ የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ የውሳኔ ሃሳብ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት አዋጁ በሙስና ምርመራ፣ በክስ አመሰራረትና ማስረጃ በማሰባሰብ ሂደት ላይ ያጋጥሙ የነበሩትን ችግሮች ለመቅረፍ ያስችላል። - ; ኮሚሽኑ በሙስና ወንጀል የተካተቱት አዳዲስ የወንጀል ድንጋጌዎች የመመርመርና የክስ አፈፃፀም በማያሻማ መልኩ እንዲከናወንና እንደዚሁም በአፈፃፀም ሲያጋጥሙት የነበሩትን የግልፅነት መጓደል ችግሮች ለማስወገድ የሚያስችልና በሙስና ወንጀልነት ያካተታቸውን ድንጋጌዎች ግምት ውስጥ ያስገባ  መሆኑ ተመልክቷል ። - ; አዋጁ ከህዝብ የተሰበሰበ እንዲሁም ለህዝብ አገልግሎት ተብሎ የተሰበሰበ ሃብት በሚያስተዳድሩ የግል ዘርፎች ላይ የሚፈጸሙ የሙስና ወንጀሎች ለመከላከልና ተጠያቂ ለማድረግ በሚያስችል መልኩ ተደንግጓል ። - ; ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው ከዓለም ባንክ የተገኘውን በ38 ዓመታት የሚከፈል 675 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ብድር ለማጽደቅ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ለበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቷል። - ; የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ስምምነቱን አስመልክተው ለምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ ፕሮጀክቱ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2015 እስከ 2020 ባሉት አምስት ዓመታት ለምግብ ዋስትና ችግር ተጋላጭ በሆኑ በስምንት ክልሎች የሚገኙ 411 ወረዳዎች 10 ሚሊዮን የሚጠጉ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል ። - ; በተመሳሳይ  ምክር ቤቱ “ለአህጉራዊ የዘላቂ አርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት”  ማስፈጸሚያ ሚኒስቴሩ ከዓለም ባንክ ጋር ያደረገውን የ75 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የብድር ስምምነት ተወያይቶ ለቋሚ ኮሚቴው መርቷል። - ; ፕሮጀክቱ በሶማሌና አፋር ክልሎች ላይ ሲተገበር መቆየቱ የገለጹት ወይዘሮ ሙፈሪሃት አዲሱ ፕሮጀክትም ሁለቱን ክልሎች ጨምሮ በኦሮሚያና በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች የሚገኙ 21 የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ወረዳዎች ለተፈጥሮ ሃብት አስተዳደር፣ ለኑሮ ማሻሻያ ድጋፍ፣ ለእንስሳት የገበያ ልማት ዝርጋታና ሌሎች መሰል ተግባራት ረገድ ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል። - ; በተጨማሪም የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነርና  የእንባ ጠባቂ ተቋም ዋና እንባ ጠባቂ የስራ ዘመናቸው ዛሬ የተጠናቀቀ ሲሆን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2007 እንዲራዘም ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል ። ),
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
485
 ኮሚሽኑ በተጠርጣሪ የቀድሞ ባለስልጣናትና ነጋዴዎች ላይ ክስ መሰረተ ። የፌዴራል ስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግ በሙስና ወንጀል በተጠረጠሩ የቀድሞ ባለስልጣናትና ነጋዴዎች ላይ በስድስት ችብጦች ላይ ክስ መሰረተ ፤ አቶ ታምራት ላይኔም ከተጠርጣሪዎቹ ጋር ክስ ተመሰረተባቸው ። የኮሚሽኑ አቃቤ ህግ በፌዴራል ተቅላይ ፍርድ ቤት ክስ የመሰረተባቸው ተጠርጣሪ ባለስልጣናትና ነጋዴዎች አቶ አሰፋ አብርሃ ፣ አቶ በሻህ አዝምቴ ፣ አቶ ስዬ አብርሃ ፣ አቶ ምህረታብ አብርሃ ፣ አቶ ታምራት ላይኔ ፣ አቶ ፍስሃ አብርሃ ፣ አቶ ፍጡር ዘአብ አስገዶም ፣ ወይዘሮ ተምኒት አብርሃ ፣ ካህሳይ አባይ ፣ ዶክተር አብዲ አደም ፣ ሚስተር ህራየር ቤሄስኒሊያን እና አቶ ፍጹም ዘአብ አስገዶም ናቸው ። የፌዴራሉ ተቅላይ ፍርድ ቤቱ ዛሬ ባዋለው ችሎት አቶ አሰፋ አብርሀና አቶ ስዬ አብርሀ ወንድማቸው አቶ ምህረታብ አብርሀ ከኢትዮጰያ ንግድ ባንክ ከደንብና ስራት ውጭ ብድር እንዲያገኙ በማድረጋቸው አቶ ምህረታብም ብድሩን ያለአግባብ በመውሰዳቸው አቃቤ ህጉ ክሱን መስርቶባቸዋል ። እንዲሁም አቶ አሰፋ አብርሀ ፣ አቶ ስዬ አብርሀና አቶ ታምራት ላይኔ መንግስት ተሽከርካሪዎችን ከቀረጥ ነጻ ለማስገባት ያወጣውን ደንብ በሚጻረር ሁኔታ አቶ ካህሳይ አባይ አብርሀ አምስት የጭነት መኪናዎችን ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ እንዲያስገቡ በማድረጋቸውና አቶ ካህሳይም በህገ-ወጥ መንገድ መኪናዎችን በማስገባት ተከሰዋል ። በተጨማሪም አቶ ስዬ አብርሀና አቶ ፍጡር ዘአብ አስገዶም 10 የጭነት መኪናዎችን አቶ ምህረታብ አብርሀና አቶ ፍስሀ አብርሀ በቅናሽ ዋጋ እንዲያስገቡ በማድረጋቸውና አስገቢዎችም የተጠቀሱትን ተከሳሾች ስልጣን መከታ በማድረግ መኪኖቹ በህገ-ወጥ መንገድ በቅናሽ በማስገባታቸው የኮሚሽኑ አቃቤ ህግ ከሷቸዋል ። እንዲሁም አቶ ስዬ አብርሀና ዶክተር አብዲአደም የአቶ ስዬ እህት ወይዘሮ ተምኒት አብርሀ በህገ-ወጥ መንገድ በጤና ትበቃ ሚኒስቴር እንዲቀጠሩ በማድረጋቸው ክስ ተመስርቶባቸዋል ። አቶ አሰፋ አብርሀ ወንድማቸው አቶ ምህረተአብ አብርሀ በህገ-ወጥ መንገድ በትግራይ ክልል የተምቤን ወረዳ የሜታ አቦ ቢራን የማከፋፈል ውክልና እንዲሰጣቸው ማድረጋቸው የሚያስጠይቃቸው በመሆኑ ተከሰዋል ። እንዲሁም አቃቤ ህጉ አቶ አሰፋ አብርሀንና አቶ በሻህ አዝምቴን የከሰሳቸው የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፣ የደብረዘይት ዱቄትና የጉለሌ ሳሙና ፋብሪካዎችን ቸምሮ የሀረር ማተማያ ቤትና ታይቱ ሆቴል በሚሸጡበት ወቅት ሚስተር ህራየር ቤሄሲኒያንና አቶ ፍጹም ዘአብ አስገዶም በጨረታው አላግባብ እንዲጠቀሙ በማድረጋቸው ነው ። ችሎቱ ክሶቹን ያነበበላቸው ተከሳሾች በበኩላቸው " የስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን መቋቋም ህገ-መንግስቱን ይጥሳል ፣ የተከሰስንበት ጉዳይ የዋስትና መብት አያስከለክልም ስለዚህ የዋስትና መብታችን ይጠበቅልን " ሲሉ ተይቀዋል ። በተጨማሪ የተጠርጣሪ ተበቆች የደንበኞቻቸው የዋስትና መብት ተከብሮላቸው በተከሰሱባቸው ጉዳዮች ላይ መቃወሚያ ለመስጠት ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ችሎቱን ተይቀዋል ። አቃቤ ህግ በበኩሉ የስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ህግ በስልጣን አላግባብ በመጠቀም ወንጀል ለተጠረጠሩ ተከሳሾች የዋስትና መብት ስለሚከለክል ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን የዋስትና መብት እንዲከለክል አመልክቷል ። በመጨረሻም ችሎቱ ግራ ቀኙን ካዳመጠ በኋላ የዋስትና መብትን በተመለከተ ለተነሱት ክርክሮች ለመጪው ትቅምት 26 እንዲሁም ዛሬ ችሎት ልቀረቡ ተከሳሾችን እና የክስ መቃወሚያ ለማየት ለመጪው ህዳር 6 ቀጠሮ ሰጥቷል ። ፖሊስም በዛሬው ችሎት ያልቀረቡ ተጠርጣሪ ተከሳሾችን በመጪው የቀጠሮ ቀን እንዲያቀርብ በማዘዝ ችሎቱ የዛሬ ውሎውን ማጠናቀቁን ዋልታ እንፎርሜሸን ማእከል ዘግቧል ።
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
486
 ማኔጅመንቱ በሙስና በተዘፈቁ ስራ አስኪያጆችና ሰራተኞች ላይ እርምጃ አለመውሰዱ ተጠቆመ ። የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ አንዳንድ የቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆችና የስራ ሃላፊዎች በሙስና የተዘፈቁ መሆናቸውን ዋና መስሪያ ቤቱ እያወቀ እርምጃ ስለማይወስድ በራሳቸው ጊዜ እየለቀቁ የግል የንግድ ስራ ያካሂዳሉ ተባለ ፤ ዋና ስራ አስኪያጁ በበኩላቸው በክትትል በተደረሰባቸው ላይ እርምጃ እየተወሰደባቸው ነው ይላሉ ። አንዳንድ የባንኩ ሰራተኞችና ነጋዴዎች ሰሞኑን ለዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል እንደገለጹት አንዳንድ የባንኩ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆችና ሃላፊዎች ብድር የሚሰጡት በጥቅም ግንኙነት በመሆኑ ባንኩ በተለይም በክልል ቅርንጫፍ ባንኮች ከሚያበድረው ብድር 85 በመቶ ተመላሽ አልሆነም ። ከአዲስ አበባ ውች ካሉት 15 ቅርንጫፎች 75 በመቶ የሚሆኑት ስራ አስኪያጆች ከባንኩ ስራ ለቀው ፤ ግማሾቹ በሰበሰቡት ገንዘብ የራሳቸውን ንግድ ሲያካሂዱ ቀሪዎቹ ደግሞ በየግል ድርጅቶች ተቀጥረው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል ። በተለይም የድሬደዋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅና መሃንዲሱ ስራቸውን ለቀው እዚያው ድሬደዋ ያለምንም ተያቂ ከፍተኛ የንግድ ስራ እየሰሩ እንደሚገኙ ገልጸው ፤ በባህርዳር ፣ ወላይታ እና ወሊሶ ባንኮችም ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ ጠቁመዋል ። እንዲሁም በዋናው ባንክ አብይ ቅርንጫፍ የውጭ ባንኮች አገልግሎት ዋና ክፍል በተለይ ለአንዱ ሰራተኛ በግል አካውንቱ በቀን 100 ሺ ብር ድረስ ገቢ እንደሚሆንለት ከአንድ አመት በፊት ለባንኩ ማኔጅመንት ጥቆማ ቢቀርብም የእርምት እርምጃ አለመወሰዱን አስተያየት ሰጪዎቹ አጋልጠዋል ። በተጨማሪም በባንኩ የተያዙ የብድ መያዣ ቤቶችና መኪናዎች በአግባቡ ባለመያዛቸው ለብልሽትና ለጉዳት እየተዳረጉ መሆናቸውን የባንኩ ማኔጅመንት ቢያውቅም ለንብረቶቹ ደህንነት እርምጃ አለመውሰዱን ተቁመዋል ። የባንኩ ማኔጅመንትም በወቅቱ በቂ መረጃዎች እየደረሱት የእርምት እርምጃ ባለመውሰዱ ማኔጅመንቱም ከችግሩ ንጹህ ነው እንደሚያስብል አመልክተዋል ። የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አድማሱ ተጫኔ ተጠይቀው ፤ በባንኩ አሰራር ሙስና አለ የሚለውን የማይቀበሉት ቢሆንም በባንኩ ኦዲተሮች ክትትል የተደረሰባቸው ሰራተኞች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው ብለዋል ። የቅርንጫፍ ባንኮች ብድር አይመለስም ለሚለው አልፎ አልፎ አለአግባብ የተሰጡ ብድሮች መኖራቸውናና ባንኩ ከሰጠው ብድርና ከፕሮጀክቱ ትልቅነት አንጻር ወደ 85 በመቶ ሊደርስ እንደሚቻል ጠቁመዋል ። የባንኩ ድሬደዋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅና መሃንዲስን በተመለከተ በኦዲተሮች ክትትል እንደተደረሰባቸው መሰወራቸውን ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸው ፤ ድሬደዋ ውስጥ የሚገኙ ከሆነ ለፍርድ የማናቀርብበት ምክንያት የለም ብለዋል ። በተመሳሳይም በባህርዳር እና ወላይታ ቅርንጫፍ ስራ አኪያጆች በነበሩት ክስ መመስረቱን ተቁመው ፤ ይሁንና የወላይታው ስራ አስኪያጅ በሞት መለየታቸውን አስረድተዋል ። በዋናው ባንክ የውጭ ባንኮች አገልግሎት ዋና ክፍል ውስጥ ስለሚፈ ጸመው ሙስና ከኦዲተሮቻቸው ከአመት በፊት መረጃው እንደቀረበላቸው ገልጸው ፤ በተጨባጭ የቀረበ አለመሆኑንና ፋይሉ የተዘጋ ባይሆንም አንዱን ግለሰብ ወደ ሌላ ባንክ እንዲዛወር ማድረጋቸውን ተናግረዋል ። የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ የቦርድ አመራር ሊቀመንበር እና የመሰረተ ልማት ምክትል ሚኒስትር አቶ ሃይሌ አሰግዴን የዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል ረፖርተር ከሶስት ሳምንት በፊት መረጃውን አቅርቦ መልስ እንዲሰጡት ተደጋጋሚ ሙከራዎች ቢያደርግም መልስ አለማግኘቱን ገልጿል ።
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
487
የመከላከያ ኃይላችን ከፍተኛ አመራር ከሙስናና ፀረ ዴሞክራሲያዊ አሰራር የፀዳ እንዳልነበረ ተገለጸ በሥርዓታችን ላይ ተደቅነው የነበሩት የሙስናና ፀረ ዴሞክራሲያዊ አደጋዎች በመከላከያ ኃይላችን ውስጥ በተለያዩ ደረጃዎች የታዩና በከፍተኛ አመራር ላይ ያሉ አካላትም ከህወሓት አንጃዎች ጋር የሚተሳሰሩባቸው ገመዶች መሆናቸውን አመራር ላይ የሚገኙ ከፍተኛ መኮንኖች ገለጹ። ከፍተኛ መኮንኖቹ ትናንት በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ተገኝትው በሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከጋዜጠኞች ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሙስናና ፀረ ዴሞክራሲያዊ አካሄድ በሥርዓቱ ውስጥ የታዩና በየደረጃው ያሉ እስከሆነ ድረስ የመከላከያ ኃይላችን ከፍተኛ አመራር ከዚህ የፀዳ ነው ብሎ መናገር አይቻልም ብለዋል። በከፍተኛ አመራር ላይ የሚገኙና ከሲቪል ተቋማትም ሆነ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር በሚኖራቸው ግንኙነት ሳቢያ በዚህ የሙስና ድርጊት ውስጥ የተነካኩ አባላት መኖራቸውን ጠቁመው በመከላከያ ኃይላችን ውስጥ በተለያዩ ደረጃዎች የተፈፀሙ የሙስና ወንጀሎችን ለማጣራት አንድ ኮሚቴ መደራጀቱንና እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል። ኮሚቴው ሥራውን እንዳጠናቀቀ ወንጀለኞቹን ለሕግና ለህዝብ ማቅረቡ እንደማይቀርም አስታውቀዋል። ከሙስና ወንጀል በተጨማሪም ፀረ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን የሚያራምዱና በሰራዊቱ መካከል ግልጽ አሰራር እንዳይሰፍን ሃሳብን በነፃ ማንሸራሸር እንዳይኖር የሚያደርጉ እንደነበሩ አመልክተዋል። የመከላከያ ሠራዊታችን ሕገ መንግሥታዊ ግዴታውን ለመወጣት ጠንካራ እምነት ሊኖረውና በመካከሉ ነፃ አስተሳሰብ ሊሰፍን ይገባል ያሉት እነዚሁ ከፍተኛ መኮንኖች ፀረ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ያላቸውን ሰዎች ከአመራሩ ማንሳትና ለሥራ የሚያነሳሳ ሁኔታ መፍጠር ተገቢ ሆኖ መገኘቱን ተናግረዋል። በሰራዊቱ ውስጥ ዓይነተኛ ሚና የነበራቸውና ነገር ግን ከአዲስ አስተሳሰብና ለውጥ ጋር ሊራመዱ የማይችሉ የአመራር አባላት ከቦታው እንዲነሱ በመደረጉ አንዳንድ ወገኖች በተለይም ከህወሓት ተገንጥሎ የወጣው ቡድን አባላት የመከላከያ ኃይላችን የተዳከመ አድርገው እንደሚያስወሩ ጠቁመዋል። አያይዘውም አገራችን ሠራዊቱን በአዲስ አስተሳሰብና ለውጥ አቅጣጫ የበለጠ አቅምና ብቃት እንዲኖረው ማድረግ የሚችሉ ከፍተኛ መኮንኖች ያፈራችና ያዘጋጀች በመሆኗ የመዳከም ስጋት ፈፅሞ ሊኖር እንደማይችልም አረጋግጠዋል። በህወሓት አመራር መካከል የተፈጠረው መከፋፈል በመከላከያ ሠራዊታችን ውስጥ ያስከተለው ችግር እንደሌለ አመልክተው በሠራዊቱ ውስጥ እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ሊከሰት የሚችለው በራሱ አመራርና አደረጃጀት ላይ ችግር ሲፈጠር ብቻ ነው ብለዋል። እንደመኮንኖቹ ገለጻ ሠራዊቱን ምንም ሰው የትኛውም ድርጅት የራሱ በትር አድርጐ ሊጠቀምበት አይችልም። ከሻዕቢያ ጋር የተካሄደውን ውጊያ የመራነው እኛ ነን። እኛን ስላጣ ተከፋፍሏል የሚል አስተሳሰብ የሚያራምዱትም ለራሳቸው መጠቀሚያ ለማድረግ ሞክረው ያልተሳካላቸው አንጃዎች ናቸው ብለዋል። ሠራዊቱ ከሚጠበቅበት ሕገ መንግሥታዊ ግዴታ ውጭ ለተወሰነ ቡድን ዓላማ እንዲሰለፍ የማድድረግ ሙከራ እንደነበረ ገልጸው ይህን ለማድረግ የሚሞክርን አመራር በማግለል ጥንካሬውን ይዞ እንዲቀጥል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም አስረድተዋል። የመከላከያ ሠራዊታችን በሌላ ወገን የሚጐተት ሳይሆን በራሱ እያሰበ የሚሄድ ልምድ ያለው ነው ያሉት እነዚሁ ከፍተኛ መኮንኖች በጉልበት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ሊቀይር የሚመጣ ኃይል እስከሌለ ድረስ ግለሰቦችና ቡድኖች የሚያነሷቸውን ፖለቲካዊ ቀውሶች የሚያባብስ እንዳልሆነም አስታውቀዋል። የሠራዊቱ የበላይ አመራር አባላት ኢህአዴግ ባዘጋጀው ሰነድ ላይ ስለመወያየታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ሠራዊቱ የሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ጉዞና አቅጣጫ የሚያሰናክሉ አደጋዎችን የመከላከል ኃላፊነት እንዳለበትና ይህን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት አስቀድሞ የሥርዓቱን ጉዞ አቅጣጫ የሚጠቁመውን ሰንድ ማወቅ እንደሚኖርበት አመልክተዋል። አያይዘውም ከፍተኛ የመንግሥትና የሕዝብ አደራ የተጣለበት ይህ የመከላከያ ሠራዊት እንደሠራዊት ብቻ ሳይሆን እንደዜጋም በሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ መወያየት መብቱም ግዴታውም መሆኑን አስምረውበታል። ከሻዕቢያ ጋር የተካሄደው ጦርነት በኢትዮጵያ አሸናፊነት መጠናቀቁንና አንፀባራቂ ድል መመዝገቡን ጠቁመው፣ ለዚህ አንፀባራቂ ድል መገኘት የሕዝቡ ድጋፍ የሠራዊቱ ብቃትና የመንግሥት አመራር ወሳኝ አስተዋፅዖ ማበርከቱን የገለጹት እነዚሁ ከፍተኛ መኮንኖች ከህወሓት አመራር የወጣው አንጃ ግን ከብቁ አመራር ጋር ተያይዞ ለአሸናፊነት የሚያበቃ የውጊያ አስተሳሰብ እንዳልነበረውም ተናግረዋል። ከፍተኛ መኮንኖቹ አያይዘውም አፈንጋጩ ቡድን ሻዕቢያ የተደመሰሰው በእኛ አመራር ነው ማለቱ የሕዝብን ታሪክ መንጠቅና ማደናገር ካልሆነ በስተቀር ለድል የሚያበቃ አመራር ለመስጠት የቻለ እንዳልሆነ በማዕከልና በግንባር የነበረው አመራር የሚያውቀው ሐቅ ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት መከላከያ ሠራዊታችን እንደሀገር መከላከያ ሠራዊትነቱ ከሕዝቡና ከመንግሥት የተቀበለውን ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን የመጠበቅ አደራ ለመወጣት በሚያስችል አቅም ላይ እንዳለ አመልክተው በተለያዩ አጋጣሚዎች የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመፃረርና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለመፈታተን የሚሹ ኃይሎችን ለመከላከል ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
488
ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ በሚደርግ ጥረት የሚጠበቅብንን ድርሻ እንወጣለን - የትግራይ ማእከላዊ ዞን ነዋሪዎች ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ በሚደርግ ጥረት የሚጠበቅባቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የትግራይ ማእከላዊ ዞን ነዋሪዎች አስታወቁ። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ሃሳቦች የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት ለማፋጠን ለተጀመረው ጥረት ስኬታማነት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥሩም ተናግረዋል፡፡ በአድዋ ከተማ የ07 ቀበሌ ነዋሪ አቶ ገብረ ተንሳይ ክፍሎም እንደተናገሩት የአገርና የህዝብን ሃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋልና የህብረተሰቡ ፍትሓዊ ተጠቃሚነት የበለጠ ማረጋገጥ የአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ትኩረት መሆን አለበት። ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ መንግስት በሚያደርገው ጥረትም የሚጠበቅባቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡ በየአካባቢው የሚታየውን የመልካም አስተዳደር ችግር በመፍታትና ለህብረተሰቡ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ በመስጠት የአገሪቱን ሰላምና ዴሞክራሲ ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ በዞኑ በናዕዴር ዓዴት ወረዳ የ‘‘ማይጥምቀት‘‘ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አለም ሓለፎም በበኩላቸው አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ሃሳቦች የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት ለማፋጠን ለተጀመረው ጥረት ስኬታማነት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩ ናቸው፡፡ ለዚሁ የለውጥ ንግግር ተግባራዊነት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም አረጋግጠዋል፡፡ በአክሱም ከተማ የ‘‘ማዕበል‘‘ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ሓየሎም ገብረመስቀል እንዳለውም፣ አገሪቱን ካጋጥጠማት ወቅታዊ ችግር ተላቃ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንና ዜጎች በየትኛው አከባቢ ተንቀሳቅሰው የመስራት ህገ መንግስታዊ መብታቸው እንዲከበር ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ብዙ ይጠበቃል። በታሕታይ ማይጨው ወረዳ የውቅሮ ማራይ ከተማ ነዋሪ ወጣት ለምለም ትኩእ በበኩሏ በሙስናና ብልሹ አሰራር ላይ የተጀመረውን ትግል በማጠናከር የህዝቦችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልፃለች።
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
489
ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ ለማፍራት እንደሚሰሩ መምህራን ገለጹ ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ ለማፍራት እንደሚሰሩ መምህራን ገለጹ መቀሌ የካቲት 20/2010 ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ ለማፍራት የድርሻቸውን እንደሚወጡ አስተያየታቸውን የሰጡ የትግራይ ሰሜናዊና ምስራቃዊ ዞኖች መምህራን ገለጹ። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተማሪዎች በበኩላቸው በፀረ ሙስና ትግሉ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል ። ከሁለቱ ዞኖች ለተውጣጡ ከ2 ሺህ በላይ መምህራንና ተማሪዎች በስነ ዜጋ፣ ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ላይ አተኩሮ በመቀሌ ከተማ የተዘጋጀ የአምስት ቀን ስልጠና ትላንት ተጠናቋል። በውቅሮ ከተማ የአንድነት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር ተሾመ ለገሰ በሰጡት አስተያየት ከስልጠናው ያገኙት ግንዛቤ በመልካም ስነ ምግባር የታነጸ ዜጋ ለማፍራት የሚያስችል ተጨማሪ አቅም ፈጥሮላቸዋል። ለተማሪዎቻቸው መልካም ስነ ምግባር በማስተማር ሙስና የሚፀየፍ ትውልድ ለማፍራት የድርሻቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል። በክልተ አውላዕሎ ወረዳ የደንጎሎ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የስነ ምግባር መምህርት እዝግሃሪያ ገብረተኽለ በበኩላቸው፣ ስልጠናው ለተማሪዎቻቸው የተሻለ ግንዛቤ ለመፍጠር የሚያስችል ተጨማሪ አቅም እንደሆናቸው ተናግረዋል። " ሙስናን የማይሸከም በመልካም ስነ ምግባር የታነፀ ዜጋ ለማፍራት የበኩሌን እወጣለሁ " ብለዋል ። በውቅሮ ከተማ የአልሻዳይ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የስምተኛ ክፍል ተማሪ ዮርዳኖስ ኃይለማርያም ሙስናን መከላከልና መቆጣጠር የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን ተናግራለች። "የህዝብና የአገር ሃብትና ንብረት ከሙስና መከላከል የሚቻለው ራስን ከድርጊቱ በማጽዳት ነው" ያለችው ተማሪ ዮርዳኖስ፣ በፀረ ሙስና ትግሉ ለማሳተፍ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለች ። የክልል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ወልደገብርኤል ወልደማርያም በበኩላቸው እንዳሉት በክልሉ ሙስናን የሚጠየፍና ከድርጊቱ የጸዳ ትውልድ ለማፍራት እንዲቻል ትምህርት ቤቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው። በስልጠናው ከ400 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከሁለት ሺህ በላይ መምህራንና ተማሪዎች ተሳትፈውበታል።
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
490
ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስቆም እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል - የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ነዋሪዎች ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስቆም እየተደረገ ያለው ጥረት ሁሉንም ባሳተፈ መልኩ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ነዋሪዎች ጠየቁ፡፡ ባለፉት 6 ወራት በሙስና የተመዘበረ ከ52 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግስት እንዲመለስ መደረጉን የኦሮሚያ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ገልጿል። ነዋሪዎቹ ጥያቄውን ያቀረቡት “ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል የክልላችንን ልማት እናፋጥን” በሚል መሪ መልእክት በጭሮ ከተማ የፓናል ውይይት በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡ በውይይቱ ላይ የተሳተፉት አንዳንድ ነዋሪዎች እንዳሉት የህብረተሰቡ የልማት ተጠቃሚነት የበለጠ እንዲረጋገጥ መንግስት ሙስናን እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ነው ያሉት፡፡ በተለይ ለመልካም አስተዳደር እጦት ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በመለየት አፋጣኝ መፍትሄ መስጠት እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ኡመር ሀቢበ በሰጡት አስተያየት ''ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተጀመሩት የልማት ስራዎች አበረታች ቢሆኑም ከሙስናና ብልሹ አሰራር ጋር ተያይዞ በአንዳንድ አካባቢዎች የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ብዙ ሊሰራ ይገባል'' ብለዋል፡፡ ከጥልቅ ተሀድሶው በኋላ የመጡትን አበረታች ለውጦች አጠናክሮ በማስቀጠል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ማረጋገጥ ይገባል ያሉት ደግሞ አቶ ተካበ በቀለ ናቸው፡፡ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመዋጋት በሚደረግ ጥረትም የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡ የኦሮሚያ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የኮሚኒኬሽን የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ መለስ አባይነህ በውይይቱ ላይ እንደገለፁት በዘንድሮው የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ከአንድ ሺህ 200 በላይ የሙስናና ብልሹ አሰራር ጥቆማዎች ለኮሚሽኑ ደርሰውታል፡፡ እነዚህ ጥቆማዎችን በማጣራት በግለሰብ አጥፊዎች ላይ ኮሚሽኑ ክስ መስርቶ ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ማድረጉን ተናግረዋል። በሙስና የተመዘበረ ከ52 ሚሊዮን 455 ሺህ 618 ብር በላይ ለመንግስት እንዲመለስ መደረጉን ተናግረዋል። በተከሳሾቹ ተወስዶ የነበረ 664 ካሬ ሜትር የከተማ ቦታ፣ አራት የመኖሪያ ቤቶችና አንድ የድርጅት ቦታም ለመንግስት እንደሚለስ መደረጉን አብራርተዋል። ሙስና እና ብልሹ አሰራር ባለበት የሀገርን ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ እንደሚይቻል የገለፁት አቶ መለስ ህብረተሰቡ ድርጊቱን ለመከላከል የጀመረውን ትግል አጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የሀገር ሽናግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ በየደረጃ የሚገኙ የአመራር አካላትና ሰራተኞች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
491
የሙስና ወንጀል ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ ለመስጠት የአገራቱ ትብብር ሊጠናከር ይገባል የምስራቅ አፍሪካ አገራት የሙስና ወንጀል ተጠርጣሪዎችን አሳልፈው መስጠት እንዲችሉ ትብብራቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል ተባለ። የምስራቅ አፍሪካ የጸረ-ሙስና ተቋማት ኅብረት 11ኛ ጉባዔውን በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው። የኅብረቱን አባል አገራት ጨምሮ በሌሎችም የአፍሪካ አገሮች በርካታ የህዝብ ሃብት በሙሰኞች ከአንዱ ወደ ሌላው አገር እንደሚዘዋወር መረጃዎች ያሳያሉ። የምስራቅ አፍሪካ የጸረ-ሙስና ተቋማት ኅብረት የተቋቋመውም በሙሰኞች ተመዝብሮ የሚዘዋወረውን ሃብት ለመከላከል፣ ለማስመለስና ወንጀለኞችን ወንጀሉን ለፈጸሙበት አገር አሳልፎ ለመስጠት ነው። የፌዴራል የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወዶ አጦ እንደተናገሩት ሙስናን ለመዋጋት አገሮቹ በተናጠል ከመስራት ይልቅ መቀናጀት የሚችሉበት ሁኔታ ከተፈጠረ የበለጠ ውጤት ይመጣል። አገራቱ አፍሪካን ወደኋላ እያስቀሯት ከሚገኙ ምክንያቶች አንዱ የሆነውን ሙስናን ለመከላከልና የወንጀሉን ተጠርጣሪዎች አሳልፎ ለመስጠት መተባበር እንዳለባቸው ተናግረዋል። እንደ ምክትል ኮሚሽነሩ ገለጻ ከተለያዩ አገሮች በሙስና ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሃብቶችንና ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን አሳልፋ ለመስጠት አገሪቷ የምታደርገውን ጥረት ታጠናክራለች። የኅብረቱ ፕሬዚዳንት ሚስተር ቫለንቲኖ ሎንጊኖ በቀጣናው የሚደረግ የጸረ ሙስና ትግልን ለማጠናከር አባል አገራት በትብብር መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። አገራቱ በሙሰኞች የሚመዘበረውን ሃብት በጋራ በመከላከል ለዜጎቻቸው የተሻለ ኑሮ መስራት እንዳለባቸውም አክለዋል። ከየአገሮቹ የተመዘበረን ሃብት ማስመለስ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ "አሬና" የተሰኘ ማኅበር ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ኅብረቱ ከተቋቋመ ጀምሮ ከአባል አገራቱ ምርጥ ተሞክሮ በመለዋወጥ እየሰራ ሲሆን በዛሬው መድረክም ከአገራቱ ምርጥ ተሞክሮ የሚወሰድ ይሆናል። እ.አ.አ በ2007 የተመሰረተው ኅብረቱ ኢትዮጵያ፣ ታንዛንያና ኬንያን ጨምሮ ስምንት አባል አገራትን ያቀፈ ነው።
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
492
ሙስናን ለመዋጋት የሃገራት መሪዎች በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል- የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ተሳታፊዎች ሙስናን ለመዋጋትና አህጉሪቱን ከችግሩ ለማውጣት የየሃገራቱ መሪዎች በጋራና በቅንጅት መስራት ይኖርባቸዋል ሲሉ ከተለያዩ ሃገራት የተውጣጡ እና የ30ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ተሳታፊዎች አሳሰቡ፡፡ ህብረቱ በአህጉሪቱ የተንሰራፋውን ሙስና ለመከላከል የያዝነውን የፈረንጆቹ 2018 በአህጉሪቱ የፀረ ሙስና ዘመቻ አመት እንዲሆን ማወጁ ይታወሳል፡፡ ይህ የህብረቱ ውሳኔ በትክክል ተግባራዊ ተደርጎ የሚሳካ ከሆነ በአህጉሪቱ ለሁሉም ችግሮች መንስዔ የሆነውን ሙስናን መቀነስ እንደሚቻል ነው የጉባዔው ተሳታፊዎች የገለጹት፡፡ በጉባዔው ላይ የተሳተፉት የቡርኪናፋሶው ተወካይ በአህጉሪቱ ለሚስተዋሉ ግጭቶች፣ ረሃብና የከፋ ድህነት ዋነኛው መንስዔ ሙስና ነው ብለው ሙስናን መከላከል ደግሞ ከመሪዎች መጀመር ይኖርበታል ብለዋል፡፡ ሌላኛው የጉባዔው ተሳታፊ ግብጻዊ በበኩላቸው ሙስና ከደቡብ አፍሪካ እስከ ግብጽ እንደ ካንሰር የተንሰራፋ የአህጉሪቱ ችግር ነው ሲሉ ገልጸውታል፡፡ አያይዘውም ሙስና እጅግ በርካታው የአህጉሪቱ ህዝብ በድህነት ውስጥ ሳለ ጥቂቶች ብቻ ሃብቱን የሚዘርፉበት ነው ብለው ይህን ለመግታት የተደረገ ጥረት አለመኖሩ ሙስናው አሁን ለደረሰበት አስከፊ ደረጃ አድርሶታል፡፡ በመሆኑም የየሃገራቱ መሪዎች ከልባቸው ሆነው ሊታገሉት እንደሚገባ አስምረውበት ሃሳባቸውን አጠቃለዋል፡፡ የማዕከላዊ አፈርካዋ ተሳታፊ ደግሞ አፍሪካ ከፍተኛ የተፈጥሮ ሃብት የታደለች ብትሆንም አለመታደል ሆኖ አብዛኛው ህዝቧ ከድህነት ወለል በታች ይገኛል ካለች በኋላ ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ምክንያት ሙስና እንደሆነም ገልጻለች፡፡
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
493
ጸረ ልማትና ዕድገት የሆነውን ሙስናን በመዋጋት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ተግተው እንደሚሰሩ በምዕራብ አርሲ ዞን የሻሸመኔ ወረዳ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ኃላፊዎችና ሰራተኞች ማረጋገጣቸውን የወረዳው ማስታወቂያና ህዝብ ግንኙነት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ቡሽራ ያሲን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የወረዳው 30 መስሪያ ቤቶች ኃላፊዎችና ሰራተኞች በመንግስት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ላይ ያደረጉትን ውይይት ሲያጠናቅቁ ባወጡት የአቋም መግለጫ እንዳረጋገጡት ሙስናን በማስወገድ ህብረተሰቡን በአግባቡ ለማገልገል ተዘጋጅተዋል፡፡ እነዚሁ 360 የሚደርሱ ተሳታፊዎች ለሁለት ቀናት ባደረጉት በዚሁ ወይይት በአገራችን የተጀመረውን የዴሞክራሲ ስርዓት በማጠናከር የጸረ ልማት ኃይሎችን ሴራ በማክሸፍ በየተሰማሩባቸው መስኮች ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ የተያዘውን ጥረት ለማሳካት አንደሚጥሩም ገልጸዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ በቆይታቸው በልማት ስትራቴጂና ዕቅድ አተገባበር፣ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራም አፈጻጸም በሚሉና በተዛማጅ ርዕሶች ትምህርት የተሰጣቸው ሲሆን የጋራ ውይይት በማካሄድ አመቺ የአሰራር ስልቶች መቀየሳቸውን ኃላፊው አመልክተዋል፡፡
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
494
ሶማሊያ ሙስና ከተንሰራፋባቸው የዓለም ሃገራት ቅድሚያ ትወስዳለች፡- የተባበሩት መንግስታት. ባህርዳር፡ጥር 25/2010 ዓ/ም(አብመድ) ሶማሊያ ሙስና የተንሰራፋባት ሃገር በመሆኗ ለጦር ኃይሏ የምትሰጠውን እርዳታ እንደምትቀንስ አሜሪካ ባለፈው ታህሳስ ወር ማስታወቋን ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሃገሪቱ አሳሳቢ በሆነ ሙስና ውስጥ መውደቋን አረጋግጫለው ብሏል ፡፡ እንደተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መግለጫ ከሆነ ላለፉት አስርት አመታት ለሶማሊያ የሚሰጠው እርዳታ ለታለመለት አላማ ከመዋል ይልቅ ወደግለሰቦች ኪስ እንደሚገባ በጥናት ማረጋገጡን ተናግሯል፡፡ በተባበሩት መንግስታት የሶማሊያ ልዩ መልክተኛ ለአመታት የሰሩትን ጥናት አገባደው በሰጡት ሪፖርት በቅርብ ጊዜ ውስጥ በሃገሪቱ የታዩ መሻሻሎች ቢኖሩም በአመራሩ ውስጥ ሙስና መስፋፋቱ በመንግስት ግንባታ ላይ እንቅፋት እየሆነ መጥቷል ብለዋል፡፡ የሶማሊያ አስተዳደር አለመረጋጋት ለሙስና መስፋፋት እንደምክንያትነት የጠቀሱት ጥናት አቅራቢው የሙስና ወንጀልን ለመግታት እና ለማስወገድ ይቻል ዘንድ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለመመስረት ለዓመታት ያደረጉት ጥረት ምንም ዓይነት ውጤት አላስገኘም ብለዋል፡፡ "ሙስናን ያለፉት እና አሁን ያለው መንግስት ለመዋጋት ከፍተኛ ጥረት ቢደረግም የሙስና ትግሉ ከሙስና ባልጠሩ ሰዎች አማካኝነት የሚፈጸም በመሆኑ የሚፈለገውን ፍሬ ሊያፈራ አልቻለም ››ብለዋል የፖለቲካ ተንታኙ ሃሰን ሼክ ኢማም፡፡ ሼክ ኢማም እንደሚሉት ከሆነ ‹‹ሙስናን ለመታገል የፖለቲካ ቁርጠኝነቱ እዚህ ግባ የሚባል ካለመሆኑም በላይ ሙስናን ለመዋጋት የሚያስፈልጓት ተቋማት እና ስልቶች የላትም›› ብለዋል፡፡ በዚህ ረገድ ትልቅ ክፍተት መኖሩን የሚናገሩት ሼክ ኢማም ‹‹እኛ ትክክለኛና ተግባራዊ የሆነ የፍትህ ስርዓት መገንባትና የሚቋቋሙትም የፀረ-ሙስና ድርጅቶች ከየትኛውም ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነቶች ነጻ ሊሆኑ ይገባቸዋል ›› ብለዋል፡፡ ይህ ሲሆን ብቻ ነው መንግሥት ሙስናን በትክክለኛው የለውጥ ሰራዊት አማካኘነት መዋጋት እና ተልዕኮውን በድል መወጣት የሚያስችለው ብለዋል ሮይተርስ እንደዘገበው፡፡
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
495
23ኛው የፌደራልና የክልል የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ጉባኤ በሀረር ከተማ እየተካሄደ ነው ሀረር የካቲት 27/2010 ሙስናን የማይሸከምና የሚፀየፍ ዜጋ ለመፍጠር የተደረገው ጥረት አበረታች ውጤት እየታየ መሆኑን የፌደራል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ የፌደራልና የክልል የስነ ምግባርና የረሙስና ኮሚሽን 23ኛ ጉባኤ በሀረር ከተማ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ ኮሚሽነር አለልኝ ሙሉአለም በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለፁት ሙስናን የማይሸከምና የሚጸየፍ ዜጋ ለማፍራት በየደረጃው በተካሄደ ጥረት የህብረተሰቡ ግንዛቤ እየተሻሻለና ድርጊቱን እየተጋለጠ እንዲመጣ አግዟል፡፡ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ለክልል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ከ2 ሺህ 878 ጥቆማዎች ከህዝብ መድረሱ ህብረተሰቡ ምን ያህል ሙስናን እየተዋጋ እንደሚገኝ አመላካች ነው ብለዋል፡፡ ህብረተሰቡ የሙስና ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች እንዲጠየቁና ከድርጊቱ እንዲማሩ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ ኮሚሽኑ ፀረ ሙስና ትግሉን ለማጠናከር ከክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን ጋር የጋራ ስትራቴጂ እቅድ እንዲዘጋጅ አማካሪ ቀጥሮ ወደ ተግባር መግባቱንና ይህም ለጸረ ሙስና ትግሉ ትልቅ መነቃቃት የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለዚሁ ተግባራዊነትም ሁሉም አካላት የጀመሩትን ስራ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ የሀረሪ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አብዱልማሊክ በከር በበኩላቸው ''የኪራይ ሰብሳቢነት ችግርና አመለካከት ለህዳሴ ጉዞአችን እንቅፋት እየሆነ ስለሚገኝ ችግሩን ለመከላከል ኮሚሽኑና የሚመለከተው አካላት ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይጠበቃል'' ብለዋል። የክልሉ መንግስትም እነዚህን ችግሮች ለማስወገድ የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ የፌዴራል ስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የስነ ምግባር አውታሮች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ሀጎስ አብርሃ ባቀረቡት ሪፖርት ባለፉት ስድስት ወራት በተካሄደ አስቸኳይ የሙስና መከላከል ስራ ከ62 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስት ገንዘብ ከምዝበራ ማዳን ተችሏል፡፡ ገንዘቡ ግልጽነት በጎደለው የግዢ ስርአት፣ ከጨረታጋር በተያያዘና ያለአግባብ ክፍያ ሊፈፀም የነበረና በሌሎች ግልጽኝነትና ተጠያቂነትን ያልተከተለ አሰራር ሊመዘበር የነበረ ነው፡፡ ሀብት በማስመዝገብና በማሳወቅ ረገድም በግማሽ አመት በተከናወነው ስራ 1 ሺህ 827 የመንግስት ተሿሚዎች፣ ተመራጮችና ሰራተኞች ያላቸው ሀብት እንዲመዘገብ ተደርጓል። በግማሽ በጀት አመቱ ለኮሚሽኖች አቃቢ ህግ ለውሳኔ ከቀረቡ 3 ሺህ 25 መዝገቦች ውስጥ 2 ሺህ 911ዱ ውሳኔ ማግኘታቸውንና ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በቅጣት ለመንግስት ገቢ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል። በከተማው የሀረሪ ባህል ቤት አዳራሽ ትናንት በተጀመረውና ለሶስት ቀናት በሚካሄደው ጉባኤ ላይ የፌዴራልና የክልል የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ሌሎች አካላት በመሳተፈ ላይ ናቸው፡፡
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
496
የዘረፉን ሙስናና ብልሹ አሰራር ለማስወገድ ስትራቴጂክ ሰነድ አዘጋጅቶ መተግበር እንደሚገባ ተገለጸ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ የሚታየውን ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመከላከል ተቋማት ስትራቴጂክ ሰነድ አዘጋጅተው በትክክል ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው የፌዴራል የስነ - ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ በተቋማት የተቀናጀ የሙስና መከላከልና በስነ - ምግባራዊ አመራር ስትራቴጅ ሰነድ አዘገጃጀትና አተገባበር ዙሪያ ከተለያዩ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ለተውጣጡ አመራር አባላት ለሁለት ቀን የሚቆይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። በፌደራል ስነ - ምግባርና ጸረሙስና ኮሚሽን የሙስና መከላከል የጥናት ቡድን መሪ ዶክተር አሰፋ መኮንን እንደተናገሩት፤ ኮሚሽኑ ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ የስትራቴጅክ እቅድ አዘጋጅቶ ተቋማት ሙስናን ለመከላከልና ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። በዋናነት ሙስናን ለመዋጋት ለመንግስት ተቋማትና ለመንግስት የልማት ድርጅት አመራር አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት አንዱ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት ሁለት ዓመታት ኮሚሽኑ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በመለየት፣ ጥናት በማድረግ፣ የአሰራር ስርዓቶቹ ለሙስናና ብልሹ አሰራር እንዳይጋለጡ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ በርካታ የመንግስትና የህዝብን ሃብት ከብክነት ማዳን መቻሉን ጠቅሰዋል። የግንባታ ተቋማት የሚያካሂዷቸውን ግንባታዎች በተያዘለት ጊዜና በጀት አጠናቆ ያለማስረከብ፣ የግንባታ የጥራት ደረጃ ዝቅተኛ መሆን፣ ሙስናና ብልሹ አሰራሮች እንዲሁም የባለሙያ ክህሎት ማነስ የዘርፉ ዋነኛ ተግዳሮቶች እንደሆኑ የጠቆሙት ዶክተር አሰፋ፤ ተግባራቱ እንዳይፈጸሙ የመከላከል ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራው ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ ቢሰራም በአንዳንድ ተቋማት በሚፈለገው ደረጃ የተጠናከረ ባለመሆኑ "ከዚህ በላይ መስራትን ይጠይቃል" ብለዋል። የኮንስትራክሽን ዘርፉን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት ተቋማት የሙስና መከላከያ ስትራቴጅክ እቅድ በማዘጋጀትና በመተግበር ሙስናን መከላከል እንደሚጠበቅባቸው ዶክተር አሰፋ አስገንዝበዋል። በውይይቱ ከአዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ጽህፈት ቤት ጉለሌ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የተገኙት አቶ ቴዎድሮስ መግራ በበኩላቸው፤ ለተቋም ህልውና የአመራሩ ሚና ወሳኝ በመሆኑ ብልሹ አሰራርን ለመዋጋት አመራሩ ጥረት ማድረግ እንዳለበት ተናግረዋል። በአንዳንድ የግንባታ ተቋማት ሙስናና ብልሹ አሰራር በስፋት የሚታይ ሲሆን፤ ለውሳኔ መዘግየትና ተጠያቂነትን መሸሽ በስፋት እንደሚታዩ ጠቅሰዋል። በተመሳሳይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ግርማ መኮንን፤ ስልጠናው "በስነ ምግባር የታነጸ አመራር አባል ለማፍራት ያግዛል" ብለዋል። ዘርፉ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ ለሙስናና ብልሹ አሰራር የተጋለጠ በመሆኑ ስትራተጂካዊ በሆነ መንገድ መመራት እንዳለበት የተናገሩት አቶ ግርማ አመራሩ ግንዛቤ እንዲያገኝ የተለያየ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሙስና መከላከልና በስነ_ምግባራዊ አመራር ስትራቴጅ ሰነድ አዘገጃጀትና አተገባበር የግንዛቤ ማስጨበጥ ስልጠና ባለፉት ሁለት ዓመታት ለተለያዩ ተቋማት አመራር አባላት ከዚህኛው ዙር በፊት በ27 ዙር ተሰጥቷል።
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
497
አዋጅ ቁጥር ፬፻፴፫/፲፱፻፺፯ የተሻሻለው የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ Home / አዋጅ ቁጥር ፬፻፴፫/፲፱፻፺፯ የተሻሻለው የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ አዋጅ ቁጥር ፬፻፴፫/፲፱፻፺፯ የተሻሻለው የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝቦች ሙስና እና ብልሹ አሠራር የአንድን አገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገት የሚገታ ተግባር መሆኑን የተገነዘቡ በመሆናቸው፤ አገሪቱ የተያያዘችውን የእድገት ጎዳና እና የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ለማፋጠንና ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ሙስናን እና ብልሹ አሠራርን በቁጥጥር ሥር ማዋል አስፈላጉ በመሆኑ፣ ለዚህም ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለመሸከም የማይፈልግ እና ይህንኑ በብቃት ለመዋጋት ዝግጁ የሆነ ሕብረተሰብ መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ፤ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ለመመርመር፣ ለመክሰስ ለመቆጣጠርና ለመከላከል መልካም ሥነ ምግባር በኀብረተሰቡ ውስጥ እንዲስፋፋ በማድረግ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን በብቃት መዋጋት እንዲቻል፣ የኮሚሽኑን አሰራርና እንቅስቃሴ የግልጽነትና የተጠያቂነት መርሆዎችን በሚገልጽ መልኩ እንዲሁም ኮሚሽኑ ሀላፊነቱን በተሻለ ብቃት እንዲወጣ በሚያስችለው መልኩ የኮሚሽኑን ማቋቋሚያ አዋጅ ለማሻሻል በማስፈለጉ፣ የኮሚሸኑን ስልጣንና ተግባር ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የወንጀል ህግ ጋር በተጣጣመ ሁኔታ ማሻሻል በማስፈለጉ፣ ኮሚሽኑ በከባድ የሙስና ወንጀሎች ላይ ትኩረት አድርጐ እንዲንቀሳቀስ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ ኮሚሽኑ ከሌሎች አግባብነት ካላቸው የምርመራና የአቃቤ ህግ ተቋማት ጋር ስለሚሰራበት ሁኔታ ዝርዝር ድንጋጌዎችን መደንገግ በማስፈለጉ፣ በሌሎችም ግልጽነት በሚያንሳቸው አንዳንድ የአዋጁ ድንጋጌዎች ላይ ማሻሻያዎችን ማድረግ በማስፈለጉ፣ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፶፭/፩/ መሰረት የሚከተለው ታውጆአል፡፡ ክፍል አንድ ጠቅላላ ፩. አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “የተሻሻለው የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሸን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ፬፻፴፫/፲፱፻፺፯” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ፪. ትርጓሜ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ አዋጅ ውስጥ፤ ፩. “ኮሚሽን” ማለት የፌዴራል የሥነምግባር እና የጸረሙስና ኮሚሽን ነው፡፡ ፪. “ኮሚሽነር እና ምክትል ኮሚሸነር” ማለት እንደቅደም ተከተሉ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ወይም ምክትል ኮሚሽነር ነው፡፡ ፫. “የመንግሥት መስሪያ ቤት” ማለት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል በመንግሥት በጀት የሚተዳደር እና የፌዴራል መንግሥቱ ሥራዎች የሚከናወኑበት ማናቸውም መስሪያ ቤት ነው፡፡ ፬. “የመንግሥት የልማት ድርጅት” ማለት የመንግሥት ባለቤትነት ድርሻ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ያለበት ማናቸውም የፌዴራል መንግሥት የልማት ድርጅት ወይም የአክሲዮን ኩባንያ ነው፡፡ ፭. “የመንግሥት ባለሥልጣን” ማለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባሎች፣ ከሚኒስቴር ደረጃ በላይ የሆኑ የፌዴራል መንግሥት ባለሥልጣኖች፣ ሚኒስትሮች፣ ሚኒስቴር ዴኤታዎች፣ ምክትል ሚኒስትሮች፣ ኮሚሸነሮች፣ ምክትል ኮሚሸነሮች፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች፣ የብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ም/ቤት አባሎች፣ የክልል መንግሥት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች፣ የአዲስ አበባ መስተዳድርና የድሬዳዋ መስተዳድር የምክር ቤት አባሎች፣ ከመስተዳድሮቹ ቢሮ ኃላፊዎች በላይ ያሉ ባለሥልጣኖች፣ የመስተዳድሮቹ ቢሮ ኃላፊዎች እና በተመሳሳይ ደረጃ ላይ የሚገኙ የፌዴራል፤ የክልል እንዲሁም የአዲስ አበባና የድሬዳዋ መስተዳድሮች ባለሥልጣኖችን ይጨምራል፡ ፮. “የመንግሥስ ሠራተኛ” ማለት በዚህ አንቀጽ ንሁስ አንቀጽ ፭ ውስጥ የተጠቀሱት ውጭ ያለ በፌዴራል ወይም በክልል ወይም በአዲስ አበባ መስተዳድሮ ወይም በድሬዳዋ መስተዳድር የመንግሥት መሥሪያ ቤት ወይም የልማት ድርጅት ውስጥ ተሹሞ፣ ተመድቦ፣ ተቀጥሮ፣ በህዝብ ተመርጦ የሚሰራ ሰው ነው፣ ፯. “የሥነምግባር አውታሮች” ማለት በመንግሥት አስተዳደር ውስጥ ምግባረ ብልሹ ባህርያትን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ እና ሙያዊ ብቃትን እና መልካም ሥነምግባርን ለማበረታታት የሚያገለግሉ ዘዴዎች፣ አካላት ሥርዓቶች ወይም አስፈላጊ ሁኔታዎች እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ ፰. “ከባድ የሥነምግባር መጣስ” ማለት አግባብ ባለው የሥነምግባረ ደንብ መሠረት ከሥራ ሊያስናብት የሚተል ጥፋት ነው፡፡ ፱. “ከባድ የሙስና ወንጀል” ማለት፣ ሀ. ከፍተኛ ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ ባላቸው የመንግሥት መስሪያ ቤቶችና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ላይ የሚፈጸሙ ከፍተኛ የገንዘብ መጠንን ያካተቱ የሙስና ወንጀሎች ወይም፣ ለ. የመንግሥት ባለሥልጣንን የሚመለከቱ የሙስና ወንጀሎች ወይም፣ ሐ. በአገር ሉአላዊነት፣ ኢኮኖሚ፣ ጸጥታ እንዲሁም በሕብረተሰቡ ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሱ ወይም ሊያደርሱ የሚችሉ የሙስና ወንጀሎች ናቸው፡፡ ፲. “የባንክ ሂሳብ” ማለት በባንክ የተቀመጠ ገንዘብ፣ ወርቅና የመሳሰሉት ውድ እቃዎች እንዲሁም አንድ ደንበኛ ከባንኩ ጋር የሚያደርጋቸውን ማናቸውንም ግንኙነቶች/ትራንዛአክሽኖች/ የሚየጠቃልል ነው፡፡ ፲፩. “ሰው” ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው፡፡ ክፍል ሁለት ስለኮሚሹኑ መቋቋም እና ሥልጣንና ተግባር ፫. የኮሚሸኑ መቋቋም ፩. የፌዴራል የሥነምግባር እና የጸረ-ሙስና ኮሚሽን /ከዚህ በኋላ ኮሚሽኑ እየተባለ የሚጠራ/ ራሱን የቻል የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤት ሆኖ በዚህ አዋጅ መሠረት ተቋቁሟል፡፡ ፪. የኮሚሽኑ ተጠሪነት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሆናል፡፡ ፬. ስለኮሚሽኑ የአሠራር ነፃነት በዚህ አዋጅ በአንቀጽ ፫ ንዑስ አንቀጽ ፪ የተደነገገው ቢኖርም ኮሚሽኑ በሚመረምራቸው ወይም ክስ በሚመሰርትባቸው ወይም ክስ በመሰረተባቸው ጉዳዮች ላይ ከማንኛውም ሰው ወይም አካል ጣልቃ ገብነትና አመራር ነፃ ነው፡፡ ፭. ዋና መስሪያ ቤት የኮሚሽኑ ዋና መስሪያ ቤት አዲስ አበባ ይሆናል፡፡ ሆኖም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በየክልሉ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶችን ሊያቋቁም ይችላል፡፡ ፮. የኮሚሽኑ ዓላማዎች ኮሚሽኑ የሚከተሉት ዓላማዎች ይኖሩታል፡፡ ፩. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የሥነ ምግባር እና የጸረ ሙስና ትምህርቶችን በማስፋፋት የነቃ እና ሙስናን ሊሸከም የማይችለ ሕብረተሰብ እንዲፈጠር ጥረት ማድረግ፣ ፪. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የሙስና ወንጀልን እና ብልሹ አሠራርን መከላከል፤ ፫. የሙስና ወንጀልን እና ብልሹ አሠራርን ማጋለጥ፤ መመርመር እና መክሰስ፣ ፯. የኮሚሽኑ ስልጣንና ተግባር ፩. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር ስለሙስና ጎጂነት የህዝቡ ንቃተ ህሊና እንዲጎለብት በማስተማር እና መልካም ሥነ-ምግባር በሕዝብ አገልግሎት እና በኀብረተሰቡ ውስጥ እንዲስፋፋ በማድረግ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን መዋጋት፤ ፪. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር በመንግስት መ/ቤቶተ እና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ውስጥ ለሙስናና ለብልሹ አሰራር የተጎለጡና ሊጋለጡ የሚችሉ የአሰራር ሥርዓቶችን በማጥናት ወይም እንዲጠኑ በማድረግ እንዲሻሻሉ ማማከርና ማሳሰብ፣ የአሰራር ስርዓቶቹ የተሻሻሉ መሆናቸውን መከታተል እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ተገቢ የሆነው እርምጃ እንዲወሰድ ወይም ውሣኔ እንዲሰጥ አግባብ ላለው አካል በማሰወቅ ወይም በማሳሰብ ሙስናን የመከላከል፣ በሌሎች ሰዎች ሲጠየቅ ተመሳሳይ ምክርና ድጋፍ የመሰጠት፤ ፫. በመንግሥት መ/ቤቶች እና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ውስጥ ከባድ የሥነምግባር መጣስ ስለመፈጸሙ ጥቆማ ሲደርሰው ወይም በቂ ጥርጣሬ ሲኖረው የማጣራት ወይም እንዲጣራ የማድረግ እና ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድ የመከታተል፤ ፬. በመንግሥት መ/ቤቶች ወይም በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ወይም ፌዴራል መንግስቱ ለክልሎች ከሚሰጠው ድጎማ ጋር በተያያዘ በክልለ መ/ቤቶች በወንጀል ህግ እና በሌሎች ሕጎች ውስጥ የተመለከቱት የሙስና ወንጀሎች በመንግስት ሠራተኞች ወይም ባለስልጣኖች ወይም በሌሎች ሰዎች ስለመፈጸማቸው ጥቆማ ስደረስው ወይም በቂ ጥርጣሬ ሲኖረው የመመርመርና የመክሰስ ወይም እንዲመረምር ወይም እንዲከሰስ የማድረግ፤ ፭. ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ በቂ ጥርጣሬ ሲኖረው በማናቸውም ባንክ የሚገኝ የተጠርጣሪዎች የባንክ ሂሳብ በኮሚሽነሩ ትእዛዝ እንዲመረመር የማድረግ፣ መረጃ የማግኘት እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በፍርድ ቤት ትእዛዝ እንዲከበር የማድረግ፣ ፮. ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዝ በምርመራ ላይ ያሉ ሰዎች ሀብት በፍርድ ቤት ትእዛዝ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ፣ በሙስና ወንጀል የተገኘ ለመሆኑ የተረጋገጠን ወይም በመስና ወንጀሉ ከተገኘው ጥቅም ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ማናቸውንም ንብረት ወይም ሀብት በፍርድ ቤት ትእዛዝ እንዲወረስና በሐራጅ ተሸጦ ወይም ሳይሸጥ ለመንግሥት ገቢ እንዲሆን የማድረግ፣ ፯. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በህግ በሚደነገገው መሠረት የመንግሥት ባለስልጣኖችን እና በህግ ሀብታቸውንና የገንዘብ ጥቅማቸውን እንዲያስመዘግቡ ግዴታ ያለባቸውን የመንግሥት ሰራተኞች ሀብትና የገንዘብ ጥቅሞች መዝግቦ የመያዝ ወይም ተመዝግበው እንዲያዙ የማድረግ፣ ፰. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር ለሙስና ወንጀል ጠቋሚዎችና ምስክሮች የአካልና የሥራ ዋስትና ጥበቃ የሚሰጥበትን ሁኔታ ማመቻቸት፣ በህግ በሚወሰን መሰረት ጥበቃ የመስጠት፣ ፱. ሙስና በመታገል እና በመከላከል ረገድ ጥሩ ውጤት ያስገኙ ሰዎችን እና መ/ቤቶችን አወዳድሮ ለሽልማት የሚበቁበትን ሥርአትና መለኪያ የመዘርጋት፣ ሲፀድቅም ተግባራዊ የማድረግ፣ ፲. የሕግ አውጪና የዳኝነት አካላት ሳይጨምር ለመንግስት መስሪያ ቤቶችና ለመንግስት የልማት ድርጅቶች የሚያገለግሉ የሥነ ምግባር ደንቦች መዘጋጀታቸውን ማረጋገጥ ወይም ማዘጋጀት እና አፈጻጸማቸውን የመከታተል፣ ከሕግ አውጭ እና ከዳኝነት አካላት ጥያቄ ሲቀርብለት በሥነምግባር ደንብ አዘገጃጀት ረገድ ምክር የመስጠት፤ ፲፩. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የሥነምግባር አውታሮችን የማስተባበር፤ ፲፪. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የሥነምግባርን እና ሙስናን በተመለከተ ጥናትና ምርምር የማድረግ እና ተመሳሳይ ሥራዎችን የመደገፍ፣ የኮሚሽኑን አላማዎች ለማራመድ የሚረዱ ሪፖርቶችን እና ቴክኒካዊ ጥናቶችን አሳትመ የማሰራጨት፤ ፲፫. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የጸረሙስና ህጎች መከበራቸውን የመከታተል እና የማረጋገጥ ስለአፈጻጸማቸው የምክር አገልግሎት የመስጠት፤ ፲፬. በመንግሥት መስሪያ ቤቶችና የልማት ድርጅቶች ውስጥ የስነምግባር መከታተያ ክፍሎች እንዲቋቋም ድጋፍ የማድረግ፤ ፲፭. ለክልሎች አስፈላጊውን የምስክርና የድጋፍ አገልግሎት የመስጠት፤ ፲፮. ተመሳሳይ አላማ ካላቸው አገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ አካላት ጋር ግንኙነትና ትብብር የመፍጠር፤ ፲፯. የንብረት ባለቤት የመሆን፣ ውል የመዋዋል፤ በራሱ ስም የመክሰስና የመከሰስ፤ ፲፰. በሕግ የሚሰጡትን እና ዓላማውን ከግብ ለማድገስ የሚረዱ ሌሎች ተግባራትን የማከናወን፡፡ ፰. በሌሎች አካላት ስለሚደረግ የሙስና ወንጀል ምርመራ ፩. ኮሚሽኑ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፯ ንዑስ አንቀጽ ፬ ከተሰጠው ሥልጣን ውስጥ ከባድ ያልሆነ የሙስና ወንጀልን የመመርመር ጠቅላላ ውክልና በሙሉ ወይም በከፊል እንደሁኔታው ለፌዴራል ወይም ለክልል የወንጀል መርማሪ አካላት ሊሰጥ ይችላል፡፡ ፪. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፩ መሠረት ውክልና ያልተሰጠው ማንኛው ወንጀልን ለመመርመር ስልጣን ያለው የፌዴራለ ወይም የክልል መንግሥታዊ አካል በዚህ አዋጅ በአንቀጽ ፯ ንዑስ አንቀጽ ፬ በኮሚሽኑ የስልጣን ክልል ስር የሚወድቅ የሙስና ወንጀል ለመፈጸሙ ጥቆማ ሲደርሰው ወይም በቂ ጥርጣሬ ሲኖረው ምርመራ መጀመር ይኖርበታል፡፡ ሆኖም ስለተጀመረው መርመራ ለኮሚሽኑ ሳይዘገይ ያሳውቃል፡፡ ፫. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፪ በተመለተው መሰረት ኮሚሽኑ ሪፖርት ሲደርሰው፡- ሀ. ጉዳዩን እራሱ ወስዶ ይመረምራል ወይም ለ. ከባድ የሙስና ወንጀልን ጨምሮ ምርመራው ሪፖርት ባደረገው የምርመራ አካል ወይም በሌላ አካል እንዲከናወን ሊያደርግ ይችላል፡፡ ፬. ኮሚሽኑ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፪ መሰረት በሚቀርብለት ሪፖርት መሰረት መልስ ሳይሰጥ ከቀረ ምርመራውን የጀመረው አካል የተጀመረውን ምርመራ በማጠናቀቅ የምርመራ ፋይሉን ክስ ለመመስረት ስልጣን ላለው አካል ያስተላልፋል፡፡ ፭. ኮሚሽኑ በቀጥታ በሚደረስው ጥቆማ ወይም በሌላ መልኩ በሚያገኘው መረጃ መሰረት የጀመራቸውን የመስና ወንጀል ምርመራዎች በሌሎች የምርመራ አካላት ወንጀል ምርመራዎች በሌሎች የምርመራ አካላት እንዲመረመር ሊያደርግ ይችላል፡፡ ማንኛውም በዚህ ንዑስ አንቀጽ መሰረት የምርመራ ፋይል የተላለፈለት አካል ምርመራውን ማከናወን ይኖርበታል፡፡ ፮. በዚህ አንቀጽ ከንዑስ አንቀጽ ፪ እስከ ፭ በተመለተው መሠረት በሌሎች የምርመራ አካላት ስለሚከናወኑ የሙስና ወንጀል ምርመራዎች ሪፖርት ስለሚደረግበት ሁኔታ ኮሚሽኑ ዝርዝር መመሪያ ያወጣል፤ ለሚመለከታቸው የምርመራ አካላት ያሳውቃል፡፡ ፱. በሌሎች የፍትህ አካላት የሙስና ወንጀል ክስ ስለመመስረት ፩. ኮሚሽኑ ከአቃቤ ሕግነት ስልጣኑ ውስጥ አግባብነት ላለው የፌዴራል ወይም የክልል አቃቤ ሕግ ወይም የስነምግባርና የጸረ ሙስና ተቋም በሙሉ ወይም በከፊል ውክልና ሊሰጥ ይችላል፡፡ ፪. ከፌዴራል መንግስት ለክልል መንግስታት ከተሰጠ የበጀት ድጎማ ጋር በተያያዘ የክልል የስነምግባርና ጸረሙስና ተቋም ወይም ስልጣን ያለው አቃቤ ሕግ ክስ መመስረት ይችላል፡፡ ሆኖም ኮሚሽኑ አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው በማንኛውም ጊዜ የክልሉን የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ተቋም ወይም አቃቤ ሕግ በመተካት በክርክሩ ውስጥ ሊገባ ይችላል፡፡ ፲. የኮሚሽኑ አቋም ኮሚሽኑ፣ ፩. በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት በተወካዮች ምከር ቤት የሚሾም አንድ ኮሚሽነር፤ ፪. በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚሾም አንድ ምክትል ኮሚሽነር እና ፫. ለሥራው አስፈላጊ የሆኑ ሠራተኞች፣ ፲፩. የኮሚሽኑ አቃቤ ሕግ አደረጃጀት የኮሚሽኑ አቃቤ ሕግ ሙያዊ ነጻነቱን ለመጠበቅ በሚያስችል መልኩ ነጻ ሆኖ ይደራጃል፡፡ ፲፪. የኮሚሽነሩ ሥልጣንና ተግባር ፩. ኮሚሽነሩ የኮሚሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በመሆን የኮሚሽኑን ሥራዎች ያደራጃል፣ ይመራል፤ ያስተዳድራል፤ ፪. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /፩/ አነጋገር እንደተጠበቀ ሆኖ ኮሚሸነሩ፣ ሀ. በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፯ የተዘረዘሩትን የኮሚሽኑን ሥልጣንና ተግባራት በሥራ ላይ ያውላል፤ ለ. በዚህ አዋጅ በተመለተው መሰረት እና የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግ አጠቃላይ መርሆዎችን መሠረት በማድረግ በሚወጣው የአስተዳደር ደንብ መሠረት የኮሚሸኑን ሠራተኞች ይቀጥራል፤ያስተዳድራል፤ ያሰናብታል፡፡ ሐ. ኮሚሽነሩ በዚህ ሕግ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግ አጠቃላይ መርሆዎችን መሠረት በማድረግ የኮሚሽኑን የአስተዳደር ደንብ አዘጋጅቶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀርባል፡፡ ሲፈቀድም በሥራ ላይ ያውላል፡፡ መ. የኮሚሽኑን ዓመታዊ የሥራ ፕሮግራም እና በጀት አዘጋጅቶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀርባል፤ ሲፈቀድም በሥራ ላይ ያውላል፡፡ ሠ. ለኮሚሽኑ በተፈቀደለት በጀት እና ባዘጋጀው የሥራ ፕሮግራም መሰረት የፋይናንስ ሕግን ተከትሎ ገንዘብ ወጪ ያደርጋል፡፡ ረ. በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎችን የኮሚሽኑ ሠራተኞች በህግ መሠረት ለመመርመር፣ ለመክሰስ ወይም ለማሰር እንዲችሉ ሥልጣን ይሰጣል፡፡ ሰ. ምርመራው በመከናወን ላይ ሳለ ጉዳይ አግባብነት ያለው በሆነ ጊዜ የማንኛውም ሰው ወይም ድርጅት የባንክ ሂሳብ እንዲፈተሽ እና አስላጊውን መረጃ እንዲሰበሰብ ትእዛዝ ለመስጠት ይችላል፡፡ ሸ. ኮሚሽኑ ከሦስተኛ ወገኖች ጋር በሚደርጋቸው ግንኙነቶች ኮሚሰኑን ይወክላል፡፡ ቀ. የኮሚሽኑን ጠቅላላ የሥራ አፈጻጸምና የሂሳብ ሪፖርት አዘጋጅቶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀርባል፡፡ ፫. ኮሚሽነሩ ለኮሚሽኑ ሥራ ቅልጥፍና በሚያስፈልግ መጠን ሥልጣነና ተግባሩን በከፊል ለኮሚሽኑ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በውክልና ሊያስተላልፍ ይችላል፡፡ ፲፫. የምክትል ኮሚሽነሩ ሥልጣንና ተግባር ፩. ምክትል ኮሚሽነሩ፣ ሀ. የኮሚሽኑን ተግባሮች በማቀድ፣ በማደራጀት፣ በመምራትና በማስተባበር ኮሚሽነሩን ይረዳል፡፡ ለ. በኮሚሽኑ መዋቅር መሰረት የሥራ ክፍፍል በማድረግ ከኮሚሽኑ ዘርፎች ከፊሉን ይከታተላል፡፡ ሐ. ኮሚሽነሩ በማይኖርበት ጊዜ እሱን ተክቶ ይሰራል፡፡ መ. ከኮሚሽነሩ ተለይተው የሚሰጡትን ሌሎች ተግባሮች ያከናውናል፡፡ ፪. ምክትል ኮሚሽነሩ ተጠሪነቱ ለኮሚሽነሩ ይሆናል፡፡ ፲፬. የኮሚሽነሩና የምክትል ኮሚሽነሩ የሥራ ዘመንና ከሥራ መነሳት ፩. የኮሚሽነሩና የምክትል ኮሚሽነሩ የሹመት ዘመን ለስድስት ዓመት ይሆናል፤ ሆኖም አስፈላጊ ሲሆን እንደገና ሊሾም ይችላል፡፡ ፪. ኮሚሽነሩ ወይም ምክትል ኮሚሽነሩ ከዚህ በታች በተመለከቱት ሁኔታዎች ካልሆኖ በስተቀር የተሾመበት የሥራ ዘመን ከማለቁ በፊት ከፈቃዱ ውጭ ከሥራው አይነሳም፤ ሀ. አግባብነት ባለው የስነምግባር ደንብ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች ተላልፎ ሲገኝ፤ ለ. ጉልህ የሆነ የሥራ ችሎታና ቅልጥፍና የሌለው ሲሆን፤ ሐ. በህመም ምክንያት ተግባሩን በተገቡው ሁኔታ ማከናወን የማይችል ሆኖ ሲገኝ፤ ፲፭. ስለኮሚሽኑ ሠራተኞች ቅጥር ሁኔታ የኮሚሽኑ ሠራተኞች የቅጥር አስተዳደር ስንብት ሁኔታ በዚህ አዋጅ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች እና የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ህግ አጠቃላይ መርሆዎችን መሠረት በማድረግ በሚወጣው የአስተዳደሩ ደንብ መሠረት ይሆናል፡፡ ፲፮. ቃለመሀላ ስለመፈጸም በኮሚሽኑ የተቀጠረ ማንኛውም ሰራተኛ ለፌዴራሉ ህገመንግሥት ታማኝ በመሆን የተጣለበትን ህዝባዊ አደራና ሙያዊ ሃላፊነት ለመወጣት ቃለመሃላ ይፈጽማል፡፡ የቃለመሃላው ዝርዝር ይዘት በአስተዳደር ደንቡ ይወሰናል፡፡ ፲፯. የኮሚሽኑ ሰራተኛ መብት ፩. ማንኛውም የኮሚሽኑ ሠራተኛ በመንግስት በሚፀድቅ የደመወዝ ስኬል መሠረት ደመወዝ ያገኛል፡፡ ፪. የማንኛውም ሠራተኛ ደመወዝ፤ ሀ. በሠራተኛው ስምምነት፤ ለ. በፍርድ ቤት ስምምነት፤ ሐ. በህግ በተደነገገው መሰረት ካልሆነ በስተቀር ሊየዝ ወይም ሊቆረጥ አይችልም፡፡ ፫. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፪/ለ/ ወይም /ሐ/ መሰረት ከሰራተኛ ደመወዝ በየወሩ የሚቆረጠው ከደመወዙ አንድ ሶስተኛ አይበልጥም፡፡ ፬. ማንኛውም የኮሚሽኑ ቋሚ ሠራተኛ በጡረታ ሕግ መሰረት የጡረታ መብት ይኖረዋል፡፡ ፭. የኮሚሽኑ ሠራተኛ፤ ሀ. ሥራውን በተገቢው መንገድ በመወጣት ላይ እያለ ለሚደርስበት ተጠያቂነት በመስሪያ ቤቱ ወጪ ድጋፍና የጥብቅና አገልግሎት ያገኛል፡፡ ዝርዝር አፈጻጸሙ በደንብ ይወሰናል፡፡ ለ. በማንኛውም አጋጣሚ የበላይ ሀላፊዎችን በአግባቡ የመጠየቅ፣ ስህተት ሲያይ የመጠቆም፣ በውይይት ችግሮችን የመፍታት እንዲሁም የስልጣን ተዋረድን ጠብቆ አቤቱታ ማቅረብ ይችላል፡፡ ሐ. በአስተዳደር ደንቡ በሚወሰን መሠረት ይግባኝ የማቅረብ መብት ይኖረዋል፡፡ መ. ከሥራው ጋር በተያያዘ ሁኔታ በሚደርስበት ጉዳት ዘላቂ ሙሉ ወይም ከፊል የመስራት ችሎታውን ያጣ የኮሚሽኑ ሠራተኛ አግባብ ባለው የጡረታ ህግ የተሰጠው መብት ይከበርለታል፡፡ ሠራተኛው ጊዜያዊ የመንግስት ሠራተኛ ከሆነና ዘላቂ ሙሉ የመስራት ችሎታውን ያጣ ከሆነ የሚከፈለው የጉዳት ካሣ መጠን የአንድ ዓመት ደመወዙ በአምስት ተባዝቶ የሚገኘው የክፍያ መጠን ይሆናል፡፡ ሠ. “ጊዜያዊ ሠራተኛ ከሆነና የደረሰው ጉዳት ዘላቂ ከፊል የመስራት ችሎታ ማጣት ከሆነ የሚከፈለው የጉዳት ካሣ መጠን በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፭ /መ/ ችሎታ ማጣቱ ደረጃ ጋር ተመጣጣኝ ይሆናል” ረ. “የደረሰበት ጉዳት ከባድ የአካል ወይም የመልክ መበላሸትን ያደረሰ ከሆነ የመስራት ችሎታ ማጣትን ባያስከትልም በዚህ አንቀጽ ድንጋጌዎች አፈፃፀም እንደዘላቂ ከፊል የመስራት ችሎታ ማጣት ይቆጠራል፡፡” ሰ. በትርፍ ጊዜው ከሥራው ጋር የጥቅም ግጭት በማይፈጥር ሥራ ላይ መስሪያ ቤቱን በማሳወቅ ለመስራት ይችላል፡፡ ዝርዝሩ ኮሚሽኑ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት ይወሰናል፡፡ ፲፰. ከግብር ነጻ ስለመሆን በዚህ አዋጅ መሠረት የሚከፈል የጡረታ አበል ወይም የጉዳት ካሣ ክፍያ ከግብር ነፃ ይሆናል፡፡ እንዲሁም በእዳ ሊከበር ወይም በማቻቻያነት ሊቀነስ ወይም ባለመብቱ ሊያስተላልፈው አይችልም፡፡ ፲፱. ከሥራ ስለማገድ ፩. የኮሚሽኑ ሠራተኛ ከሥራ ታግዶ መቆየት ለሥራው አፈፃፀም ጠቃሚ ሆኖ ከተገኘ ሠራተኛውን ከአንድ ወር ለማይበልጥ ጊዜ ከሥራና ደመወዝ አግዶ ለማቆየት ይቻላል፡፡ ፪. የኮሚሽኑ ሠራተኛ በወንጀል ወይም በዲሲፕሊን ጥፋት በህግ የተከሰሰ እንደሆነና ሲመሰከርበት ጥፋቱ ከስራው የሚያስወጣው መሆኑ ሲገመት ከስራ ታግዶ መቆየት አለበት፤ ፳. ስለይርጋ ጊዜ ፩. ቀላል የዲሲፕሊን ቅጣት የሚያስከትል ጥፋት የፈፀመ የመንግሥት ሠራተኛ የምርመራውን ጊዜ ሳይጨምር የፈፀመው ጥፋት ከታወቀበት ቀን ጀምሮ እስከ ስድስት ወር እርምጃ ካልተወሰደበት በዲሲፕሊን ተጠያቂ አይሆንም፤ ፪. ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት የሚያስከትል ጥፋት የፈፀመ የኮሚሽኑ ሠራተኛ የፈጸመው ጥፋት ከታወቀበት ቀን ጀምሮ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በጥፋቱ ካልተከሰሰ በዲሲፕሊን ተጠያቂ አይሆንም፡፡ ፫. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /፩/ ወይም /፪/ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ መውሰድ የሚገባውን የዲሲፕሊን እርምጃ ሳይወሰድ የቀረው ኃላፊ ተጠያቂ ይሆናል፡፡ ፳፩. በጀት ፩. የኮሚሽኑ በጀት በመንግስት ይመደባል፡፡ ፳፪. የሂሣብ መዛግብት ፩. ኮሚሽኑ የተሟላ እና ትክክለኛ የሂሣብ መዛግብት ይይዛል፡፡ ፪. የኮሚሽኑ የሂሣብ መዛግብት እና ገንዘብ ነክ ሰነዶች በፌዴራሉ ዋና ኦዲተር በየዓመቱ ይመረመራል፡፡ ክፍል ሦስት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ፳፫. ስለኮሚሽኑ የፖሊስነትና የዐቃቤ ሕግነት ሥልጣን ስለመመርመርና ስለመክሰስ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሥነ-ሥርዓትና በሌሎች ህጎች ለፖሊስና ለዐቃቤ ህግ የተሰጠ ሥልጣን በዚህ አዋጅ ውስጥ የተመለከቱ ጉዳዮችን በሚመለከት ለኮሚሽኑ ተሰጥቶአል፡፡ ፳፬. የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች መቋቋም ፩. በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እና ልማት ድርጅቶች ውስጥ የሥነ ምግባር ሁኔታን የሚያስተባብሩ እና ለየመስራያ ቤቶቹ የበላይ ኃላፊዎች የሚያማክሩ የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎተ ይቋቋማሉ፡፡ ፪. የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ተጠሪነቱ ለመንግሥት መሥሪያ ቤቱ ወይም ለልማት ድርጅቱ የበላይ ኃላፊ ይሆናል፡፡ ፫. የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ኃላፊ ወይም ሠራተኛን የመስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ በቅጥር፣ በእድገት ወይም በዝውውር ይመድባል፤ ለሥራ መደቡ የሚያስፈልገውን የትምህርትና የሥራ ልምድ እንዲሁም የሥነምግባር ሁኔታ በሚመለከት ከኮሚሽኑ ጋር በመመካከር ይወሰናል፡፡ ፬. የሥነምግባር መከታተያ ክፍሉ ከኮሚሽኑ ጋር የሚኖረውን የሥራ ግንኙነት በሚመለከት በዝርዝር በደንብ ይወሰናል፡፡ ፳፭. በኮሚሽንና በክልል ተቋሞች መካከል ስለሚኖረው የሥራ ግንኙነት ፩. ሙስናን መሸከም የማይችል ህብረተሰብ በመፍጠር እንዲሁም ሙስናን በመከላከል፤ በመመርመርና በመክሰስ ኮሚሽኑ ከክልል የሥነምግባር የጸረሙስና ተቋሞች ጋር በቅንጅትና በተደጋጋፊነት ይሰራል፡፡ ፪. የክልል መስሪያ ቤቶች በኮሚሽኑ በሚሰጣቸው ውክልና መሠረት የሙስና ወንጀል ጉዳዮችን ሲመረምሩና ሲከሱ ተጠሪነታቸው ለኮሚሽኑ ይሆናል፡፡ ፫. ኮሚሽኑና የክልል የሥነምግባርና የጸረሙስና ተቋሞች ለፀረሙስና እንቅስቃሴው ስኬት በጋራ የሚያከናውኗቸውን ተግባራት አፈጻጸም ለመገምገም የሚወያዩበት የጋራ ጉባኤ ሊያቋቁሙ ይችላሉ፡፡ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር የጋራ ጉባኤውን ይመራል፡፡ የጋራ ጉባኤው፤ ሀ. የጋራ የአሠራር ውስጠ ደንብ ያወጣል፡፡ ለ. ሙስናን በመከላከልና በመመርመር እንዲሁም መልካም ሥነምግባርን በማስፈን የሥራ እንቅስቃሴዎችን በመገምገም የልምድ ልውውጥ ያደርጋል፡፡ ሐ. ሥልጣንና በሚመለከት የጋራ አቅጣጫዎችን ይቀይሳሉ፡፡ መ. በኮሚሽኑ ወይም በክልል የሥነምግባርና የጸረሙስና ተቋሞች በማቀርቡ ጥናቶች ላይ ይወያያል፤ በጥናቶቹ መሠረት ሊወሰድ የሚገባቸው እርምጃዎች እንዲወሰኑ ለሚመለከታቸው አካል ያቀርባል፤ እንደሁኔታው ይወሰግል፤ በሥራ ላይ መዋላቸውን ያረጋግጣል፡፡ ፬. ኮሚሽኑና የክልል የሥንምግባርና የጸረ ሙስና ተቋሞች የጋራ ጉባኤ ያስተላለፋቸውን ውሣኔዎች መተግበራቸውን በየበኩላቸው ይከታተላሉ፡፡ ፭. የክልል የሥነምግባር የጸረ ሙስና ተቋሞች በክልላቸው ስላለው የሙስና ወንጀል ሁኔታ በሚመለከት ሪፖርትና ስታስቲክስ በየጊዜው ለኮሚሽኑ ያስተላልፋሉ፡፡ ፳፮. የሙስና ወንጀልን የማስታወቅና የመተባበር ግዴታ ፩. የመንግሥት መስሪያ ቤቶችና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች በራሳቸው የሚወሰዱት የአስተዳደር ወይም የዲሲፕሊን እርምጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ከባድ የሥነምግባር መጣስና የመስና ወንጀል የተፈጸመ ለመሆኑ ጥርጣሬ ሲኖራቸው ወዲያውኑ ለኮሚሽኑ ወይም ስልጣን ላለው የምርመራ አካል ሪፖርት የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡ ፪. ማንኛውም የመንግሥት ባለስልጣን ወይም የመንግሥት ሠራተኛ በመስሪያ ቤቱ የሙስና ወንጀል ተፈጽሞአል ወይም ሊፈጸም በዝግጅት ላይ ነው ብሎ በሚጠረጥርበት ጊዜ ስለኮሚሽኑ ወይም ሥልጣን ላለው የምርመራ አካል የማስታወቅ ግዴታ አለበት፡፡ ፫. ማንኛውም ሰው ከኮሚሽኑ ሥልጣንና ተግባር ጋር በተያያዘ ለሚጠየቀው ትብብርና ድጋፍ የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡ በተለይም ኮሚሽኑ የሙያ ድጋፍን በሚመለከት ለሚያቀርባቸው ጥያቄዎች አግባብነት ያላቸው የመንግሥት መስሪያ ቤቶችና የልማት ድርጅቶች አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠት ይኖርባቸዋል፡፡ ፬. በዚህ አዋጅ መሰረት የሙስና ወንጀል ለመመርመር ሥልጣን ያለው ማንኛውም መርማሪ በማንኛውም ጊዜ በፌዴራል ሆነ በክልል የመንግሥት መስሪያ ቤት ሥራው አግባብነት ያላቸውን መረጃዎች እንዲሰጠው ወይም እንዲመለከት መጠየቅ ይችላል፡፡ በማንኛውም በፌዴራልም ሆነ በክልል የመንግሥት መሥሪያ ቤት ወይም የልማት ድርጅት ያለ ኃላፊ ወይም ሠራተኛ የሙስና ወንጀልን ለመመርመር ሥልጣን ባለው መርማሪ ሲጠየቅ አስፈላጊውን መረጃ የማሳየት ወይም የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡ ፳፯. ቅጣት በሌላ ህግ የበለጠ የሚያስቀጣ ካልሆነ በስተቀር፤ ፩. ማንኛውም ሰው ለኮሚሽኑ፤ ለፍትሕ አካላት ወይም ለመንግሥት መሥሪያ ቤት ኃላፊ ወይም የልማት ድርጅት ኃላፊ ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ መረጃ ወይም ጉዳት ለማድረስ የሞከረ ወይም ያደረሰ ወይም ይህንኑ ሰው ለመቅጣት የሞከረ ወይም የቀጣ እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማያንስ፣ ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት እና ከስድስት ሺህ ብር በማያንስ ከሃያ አምስት ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ፪. ማንኛውም የኮሚሽኑ ኃለፊ ወይም ሠራተኛ በሕግ የተሰጠውን ሥልጣንና ኃላፊነት ያለአግባብ የተገለገለበት እንደሆነ፤ በዚያም የተነሳ ያገኘው ጥቅም መወረሱ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ከአምስት ዓመት በማያንስ፣ ከአሥራ አምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እሥራት እና ከሦስት ሺህ ብር በማያንስ፤ ከአሥር ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ፫. ማንኛውም ሰው ሆን ብሎ ኮሚሽኑን ለማሳሳት ወይም ሌላውን ሰው ለመጉዳት ሐሰተኛ ሪፖርት ጥቆማ ወይም መረጃ ለኮሚሽኑ ያቀረበ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማያንስ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራትና ከሦስት ሺህ ብር በማያንስ ከአስር ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ፬. ማንኛውም ሰው የኮሚሽኑ ሠራተኛ መስሎ በመቅረብ የማታለል ሥራ የፈጸም እንደሆነ ከሦስት ዓመት በማያንስ ከአስር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እና ከአምስት ሺህ ብር በማያንስ ከአስራ አምስት ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ፭. ማንኛውም ሰው በዚህ አዋጅ በአንቀጽ ፳፮ ንዑስ አንቀጽ ፫ ወይም ፬ በተደነገገው መሠረት ኮሚሽኑን ለመተባበር እምቢተኛ የሆነ እንደሆነ ከስድስት ወር በማያንስ ከአራት ዓመት በማይበልጥ እስራት እና ከአንድ ሺህ ብር በማያንስ ከአመስት ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ፮. ማንኛውም ሰው የኮሚሽኑን ሥራ ያደናቀፈ ወይም ለማደናቀፍ የሞከረ እንደሆነ ከሁለት ዓመት በማያንስ ከአስር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት እና ከአምስት ሺህ ብር በማያንስ ከሃያ ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ወንጀሉ የተፈጸመው ኃይል በመጠቀም የሆነ እንደሆነ ቅጣቱ በዚህ ንሁስ አንቀጽ የተደነገገው ከፍተኛ ቅጣት ይሆናል፡፡ ፯. የሙስና ወንጀል ምርመራ ሊጀምር ስለመሆኑ ወይም በምርመራ ላይ ስለመሆኑ ወይም ጉዳዩ በምርመራ ላይ መሆኑን እያወቀ ስለተፈጸመው ድርጊት ምርመራውነ ከያዘው ክፍል ፈቃድ ውጭ መግለጽ፤ መጻፍ፤ ማሰራጨት ከስድስት ወር በማያንስ ከአራት ዓመት በማይበልጥ እስራት እና ከአንድ ሺህ ብር በማያንስ ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል፡፡ ፰. ማንኛውም የመንግሥት ባለሥልጣን ወይም የመንግሥት ሠራተኛ በሚሰራበት መስሪያ ቤት የሙስና ወንጀል ስለመፈጸሙ እያወቀ ሳያውቅ መቀረት እስከ አምስት ዓመት ቀላል እስራት እና እስከ አስር ሺህ ብር መቀጮ ያስቀጣል፤፤ ፱. በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ ፩፣ ፫፣ ፬፣ ፭ እና ፮ የተመለቱት ወንጀሎች በወንጀል ህግ መሠረት ተጠያቂ በሚሆን የህግ ሰውነት ባለው ድርጅት በተፈጸሙ ጊዜ የገንዘብ ቅጣቱ አምስት እጥፍ ይሆናል፡፡ ፳፰. የመሸጋገሪያ ድንጋጌ በአዋጅ ቁ. ፪፻፴፭/፲፱፻፺፫ በሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት ተፈጽመው ምርመራቸው በሌሎች አካላት በጅምር ወይም በሂደት ላይ ያለም ሆነ የተጠናቀቁ ወይም በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያሉ የሙስና እና ከሙስና ጋር የተያያዙ የወንጀል ጉዳዮች በነበሩበት ሁኔታ ቀጥለው ውሣኔ ያገኛሉ፡፡ ፳፱. የተሻሩና ተፈጻሚነት ስለማይኖራቸው ህጎች ፩. የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረሙስና ኮሚሽን መቋቋሚያ አዋጅ ቁ. ፪፻፴፭/፲፱፻፺፫ በዚህ አዋጅ ተሽሯል፡፡ ፪. ከዚህ አዋጅ ጋር የሚቃረኑ ማናቸውም ሌሎች ህጎች በዚህ አዋጅ ውስጥ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚነት አይኖራቸውም፡፡ ፴. ደንብና መመሪያ የማውጣት ሥልጣን ፩. የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለዚህ አዋጅ አፈጻጸም ደንብ ሊያወጣ ይችላል፡፡ ፪. ኮሚሽኑ ይህንን አዋጅና በዚህ አዋጅ መሠረት የሚወጣውን ደንብ ለማስፈጸም መመሪያ ሊያወጣ ይችላል፡፡ ፴፩. አዋጁ የሚፀናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከጥር ፳፭ ቀን ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡ አዲስ አበባ ጥር ፳፭ ቀን ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. ግርማ ወልደጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
498
ሥነ ምግባር መከታተያ ክፍሎችን አሰራር ለመወሰን በወጣው የሚኒስትሮች ም/ቤት ደንብ ቁጥር 144/2000 አንቀጽ 7(3) መሰረት ከዚህ የሚከተለው የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የሥነ ምግባር መመሪያ ወጥቷል፡፡ ክፍል አንድ አጠቃላይ አንቀጽ 1. አጭር ርዕስ ይህ መመሪያ የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለሥልጣን ኃላፊዎችና ሠራተኞች “ የሥነ ምግባር መመሪያ lØ` 1/2004” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ አንቀጽ 2. ትርጓሜ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ፡- 1) “ባለሥለጣን እና ዋና ዳይሬክተር ማለት እንደ ቅደም ” “ ” ተከተላቸው የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለሥልጣንና የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ማለት ነው፡፡ 2) “ኮሚሽን ማለት የፌደራል ሥነ ምባርና ፀረ ” -ሙስና ኮሚሽን ነው፡፡ 3) “ሠራተኛ ማለት በፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች አዋጅ ” ቁጥር 515/1999 መሰረት በበባለሥልጣኑ በቋሚነት፣ ለሙከራ ጊዜ ወይም በጊዜያዊነት ተቀጥሮ በመስራት ላይ የሚገኝ የተፈጥሮ ሰው ነው፡፡ 4) “ኃላፊ ማለት በዳይሬክቶሬትና የኬዝ ቲም አስተባባሪነት ደረጃ ” ያለ የባለሥልጣኑ ባልደረባ ማለት ነው፡፡ 5) “የሥነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት ማለት የሥነ ምግባር ” ሁኔታን የሚያስተባብርና ለዋና ዳይሬክተሩ የሚያማክር በሚኒ ƒ ስሮች ደንብ ቁጥር 144/2000 መሰረት የተቋቋመ የሥራ ክፍል ማለት ነው፡፡ 6) “የሥነ ምግባር መኮንን ማለት የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለሥልጣን ” ሥነ ምግባር መኮንን ማለት ነው፡፡ 7) “ከባድ የሥነ ምግባር ጥሰት ” ማለት የሥነ ምግባር ጥሰቱ አግባብ ባለው የፌደራል መንግስት ሠራተኞች ሕግ መሰረት በዚህ መመሪያ አንቀጽ 18(2) ላይ የተመለከተውን ቅጣቶች የሚያስቀጣ ማለት ነው፡፡ 1 8) “ሰው ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በህግ ሰውነት የተሰጠው ” አካል ነው፡፡ 9) “የጥቅም ግጭት ” ማለት የባለሥልጣኑ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ወይም የቤተሰባቸው የፋይናንስ ወይም ሌላ አይነት ጥቅም ወይም ከተሰጣቸው ኃላፊነትና በሥራቸው አማካኝነት ከሚያገኙት ጥቅም ጋር በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ የሚፈጠር አላግባብ ጥቅም ነው፡፡ 10) “ሥነ ምግባር ማለት ኃላፊዎች ወይም ሠራተኞች ” ከሚሰሯቸው ሥራዎች ጋር በተገናኘ ከቅርብ ኃላፊዎች፣ ከቅርብ ሠራተኞች፣ ከበላይ የሥራ ኃላፊዎች እና ከአጠቃላዩ የመ /ቤቱ ሠራተኞች፣ ከአገልግሎት ፈላጊው ጋር ባላቸውና በሚኖራቸው ግንኙነት ሊከተሉት የሚገባ ባህሪ፣ አመለካከትና የአሰራር ሥነ ሥርዓት ነው፡፡ 11) “የሥነ ምግባር ብልሹነት ማለት ህ ” I ብረተሰቡ በመልካም ሥነ ምግባርነት ከመደባቸው ድርጊቶች እና የሥነ ምግባር መርሆዎች ጋር የሚቃረን ተግባር ነው፡፡ 12) “ጥቆማ ማለት በባለሥልጣኑ ውስጥ ስለሚፈፀም ወይም ” ሊፈፀም የታሰበን ሙስናና ብልሹ አሰራርን በራስ ተነሳሽነት ወይም በሚቀርብ ጥያቄ መሰረት የሚሰጥ መረጃ ነው፡፡ 13) “ሰነድ” ማለት በባለሥልጣኑ ይዞታ ውስጥ የሚገኝና በማናቸውም ጊዜ የተዘጋጀ ወይም የቀረበ ማናቸውም መዝገብ፣ ፋይል፣ በእጅ ወይም በማሽን የተጻፈ ረቂቅ፤ በማናቸውም የኤሌክትሮንክስ ዘዴ ተዘጋጅተው የሚታዩ፣ የሚደመጡና የሚነበቡ መረጃዎችን የሚያካትት ነው፡፡ “ምስጢር ማለት ጉዳዩ ለማይመለከታቸው ሰዎች ይፋ መደረግ ” የማይገባው መረጃ ነው፡፡ 14) “ተገልጋይ” ማለት ከባለሥልጣኑ አገልግሎት ለማግኘት የሚመጣ ማንኛውም ሰው ሲሆን ለዚህ መመሪያ አፈፃፀም ሲባል ማንኛውም ሠራተኛ በሌላ የሥራ ክፍል አገልግሎት በሚጠይቅበት ጊዜም ነው፡፡ 15) “የተሟላ ስብዕና ” ማለት ጽኑ አቋም መኖር፣ ለሥራው ያለው ጠንካራ አወንታዊ አመለካከት፣ ኃላፊነትን መሸከም መቻል፣ በራስ ተነሳሽነት የማከናወን ብቃት፣ ለሀገርና ለህዝብ መልካም ተግባራትን በራስ ተነሳሽነት የመፈጸም ጠንካራ መንፈስ መኖር፣ ራስን የመግዛትና የመቆጣጠር ችሎታ እንዲሁም የራስን ፍላጎትና ስሜት በሌሎች ላይ አለመጫን ነው፡፡ 16) “ታማኝነት” ማለት የሰዎችን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ኃላፊነትን መውሰድ፤ ከራስ ጥቅም ይልቅ የቆሙለትን ሕዝባዊ ዓላማ ማስቀደም፣ ለመንግስት ሥራ የገቡትን ቃል -ኪዳን መፈጸም፣ ህጋዊ አሰራሮችን ማስፈን፣ የሀገርን ምስጢር መጠበቅና እውነተኛ መረጃ መስጠት ነው፡፡ 17) “ግልጽነት” ማለት የባለሥልጣኑን የሕግ ማዕቀፎች፣ አሰራሩንና ተገልጋይ ሊያውቀው የሚገባውን መረጃ ባልተሸራረፈና በተሟላ መልኩ መግለጽ፣ ውሳኔዎችንም ሆነ ተፈላጊ መረጃዎችን ማወቅ የሚገባው ክፍል እንዲያውቅ ማድረግ ነው፡፡ 18) “ምስጢር መጠበቅ ” ማለት ባለሥልጣኑን፣ የሥራ ባልደረባን ወይም ተገልጋይን ሊጎዱ የሚችሉ መረጃዎችን በምስጢርነት መያዝ፣ በሙያና በሥራ ምክንያት የሚያውቁትን መረጃ እና በሕግ ምስጢር ነው ተብሎ የተደነገገን ምስጢርነቱ እስኪያበቃ ጠብቆ ማቆየት ነው፡፡ 19) “ሐቀኝነት” ማለት ከማጭበርበርና ከማታለል መራቅ፣ ኃላፊነትን ሕጋዊ በሆነ መንገድ መፈጸም፣ ሥራዎችን ትክክለኛ በሆነ አግባብ ማከናወን እና የሚያውቁትን መረጃ በትክክል መግለጽ ነው፡፡ 20) “ተጠያቂነት” ማለት አንድ ሰው ለሚፈጽመው ማናቸውም ተግባር ኃላፊ የሚሆንበት መንገድ ሲሆን ተገቢ የሆኑ ጥያቄዎች ሲቀርቡም ማብራሪያ የመስጠትና ኃላፊነትን የመውሰድ ግዴታ ነው፡፡ 21) “ለሕዝብ ጥቅም መስራት ” ማለት የህዝብን ጥቅም ማክበርና ማስጠበቅ፣ ለራስ ጥቅም አለመሯሯጥ፣ የመንግስትንና የህዝብ ንብረትን ለግል ጥቅም አለማዋል እና ከምንም በላይ ለህዝብ ጥቅም መስራት ነው፡፡ 22) “ሥልጣንን በአግባቡ መጠቀም ” ማለት ሥራን በተሰጠ ኃላፊነት መሰረት ማከናዎን ነው፡፡ 2 23) “አለማዳላት” ማለት ተገልጋይን በዘር፣ በሀይማኖት፣ በቋንቋ፣ በፖለቲካ አመለካከት ወይም በሌላ ምክንያት ልዩነት ሳያደርጉ በእኩል አይን ማየት እና በቀረበ መረጃ እና በሕግ ላይ ብቻ ተመርኩዞ አገልግሎት መስጠት ነው፡፡ 24) “ሕግን ማክበር ” ማለት አግባብ ባላቸው ሕጎችና ፖሊሲዎች መሰረት ብቻ ሥራዎችን ማከናወን፣ ሕጋዊ ትዕዛዞችን መቀበልና መፈጸም፣ ሕጋዊና ፍትሃዊ ውሳኔ በመስጠት ኃላፊነትን መወጣት ነው፡፡ 25) “ለሕዝብ ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ መስጠት ” ማለት ባለጉዳይን በጥሞና በማዳመጥ፣ በማክበርና በትህትና ለጥያቄዎቻቸው ያልዘገየና ትክክለኛ ምላሽ መስጠት ነው፡፡ 26) “አርዓያነት ማለት የመ ” /ቤትን፣ የስራ ባልደረባንና ተገልጋይን ስም ከሚያጎድፍ ተግባር መታቀብ፣ በሚሰጥ ምክርና በራስ ተነሳሽነት ትጉህ በመሆን ተከታይንና ባልደረባን በማትጋት እና በዚህ አንቀጽ ውስጥ የተዘረዘሩትን የሥነ ምግባር መርሆዎች በመተግበር ምሳሌ መሆን ማለት ነው፡፡ 27) “የዲስፕሊን ኮሚቴ ” ማለት የሠራተኛን የዲስፕሊን ጉዳዮች አጣርቶ ለመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ የውሳኔ ሃሳብ የሚያቀርብ አካል ነው፡፡ አንቀጽ 3. የተፈፃሚነት ወሰን 1. ይህ የሥነ ምግባር መመሪያ በባለስልጣኑ በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ወይም ለሙከራ ጊዜ ተቀጥረው የሚሠሩ ኃላፊዎችንና ሠራተኞችን ይመለከታል፡፡ 2. የዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህ መመሪያ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተርንና የሥነ ምግባር መኮንኑን አይመለከትም፡፡ አንቀጽ 4. የሥነ ምግባር መመሪያው ዓላማዎች የዚህ የሥነ ምግባር መመሪያ የሚከተሉት ዓላማዎች ይኖሩታል " 1. በባለሥልጣኑ የሥራ እንቅስቃሴ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ከሙስናና ብልሹ አሰራር የጸዳ እና መልካም ሥነ ምግባር የተላበሱ እንዲሆኑ ማድረግ፡፡ 2. የባለሥልጣኑን እሴቶች በመጠበቅ ራዕይና ተልዕኮውን ለማሳካት የባለሥልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች መልካም ሥነ ምግባርን ተላብሰው በቀናነት ሥራቸውን እንዲያከናውኑ ማድረግ፡፡ 3. ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሕጎችንና ደንቦችን በማክበር ሥራቸውን በሥርዓት እንዲመሩ ማድረግ፡፡ 4. ኃላፊዎችና ሠራተኞች የሕዝብ አገልጋይነትን ባህል በማዳበር ለተገልጋይ ፍትሃዊ የሆነ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ፡፡ አንቀጽ 5. ኃላፊነት 1. ኃላፊዎች ይህን የሥነ ምግባር መመሪያበሚገባ አውቀውት በስራ ላይ ለማዋል እንዲችሉ ሰራተኞችን የማስተማርና የማሳዎቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ 2. ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ይህን መመሪያ የመፈፀም ኃላፊነት አለባቸው:: 3. ኃላፊዎችና እና ሠራተኞች በመ /ቤቱ ከሥነ ምግባር ጥሰት፣ ሙስናና ብልሹ አሰራር ጋር የተያያዙ ድርጊቶች ሲፈጸሙ ለመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ፣ ለሥነ ምግባር መከታተያ ክፍል ወይም ጉዳዩ ከባድ በሆነ ጊዜ ለኮሚሽኑ የማሳወቅ ኃላፊነት አለባቸው ፡፡ ክፍል ሁለት መሰረታዊ የሥነ ምግባር መርሆዎች፣ የዲስፕሊን ጥፋቶች እና ተጓዳኝ ቅጣቶች አንቀጽ 6 የተሟላ ስብዕና የባለሥልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡- 1 .በሙያቸው አማካኝነት ከህዝቡ ጋር የሥራ ግንኙነት በሚያደርጉበት እና በሚያገለግሉበት ጊዜ የህዝቡን አመኔታ በሚጠብቅና በሚያጠናክር አኳኋን የመንግሥትን ፖሊሲ ሥራ ላይ ማዋል ይኖርባቸዋል፡፡ 2 ሥራቸውን በከፍተኛ የሙያ ሥነ ምግባር፣ ችሎታ፣ ጥበብ፣ ጥንቃቄ፣ በሙሉ ጉልበት፣ በብቃትና ውጤታማ በሆነ አኳኋን መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ 3 3 ችሎታቸው የሚፈቅደውን ያህል የተቀጠሩበትን ሥራ ማከናወን አለባቸው፡፡ 4 ተገቢ ካልሆኑ ድርጊቶች /ከአደንዣዥ እፆች ተጠቃሚነት፣ ከቁማርተኝነት፣ ከስካር፣ መጠጥ ጠጥቶ በስራ ገበታ ላይ ከመገኘትና መሰል አድራጐቶች / የራቁ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ 5 በሥራ ሰዓት በሌሎች ቢሮ ውስጥ ያለ ሥራ በመቀመጥ፣ በመስኮት በመቆም፣ በኮሪደር አካባቢም አዋኪ በሆነ አኳኋን በማውራት፣ አላስፈላጊ እንቅስቃሴ በማድረግ እና በመሳሰሉት ድርጊቶች በመረበሽ የሌሎችን የሥራ ጊዜ መሻማት የለባቸውም፡፡ 6 የቢሮ መብራት ሳያጠፉ፣ በርና መስኮት ሳይቆልፉና የተጠቀሙበትን የቧንቧ ውኃ ሳይዘጉ መሄድ የለባቸውም፡፡ 7 ከሕግ ውጭ ከመስራት ወይም ከሥነ ምግባር ብልሹነት ወይም ተገቢ ካልሆነ አድራጐት መራቅ አለባቸው፡፡ 8 በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-7) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡ - ሀ/ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር አስቸኳይ ሥራ ሲያጋጥም በዓመት እረፍት እንደየአግባቡ በትርፍ ሰዓት u ክፍያ ወይም ያለክፍያ ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጭ ሥራ ለመሥራት ፈቃደኛ አለመሆን፣.....ቀላል ለ/ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር የሠራተኛ እጥረት ወይም ክፍተት ባጋጠመ ጊዜ ተጨማሪ ኃላፊነቶችን ደርቦ ለመስራት ፈቃደኛ አለመሆን፣ .....ቀላል ሐ/ የንጽህና መገልገያ ወረቀቶችን ከተጠቀሙ በኋላ ተገቢ በሆኑ ቦታዎች ላይ አለመጣል ወይም በተዘጋጀላቸው ቅርጫት ውስጥ አለማስገባት እንዲሁም የአበባ ቦታዎችንና አረንጓዴ አካባቢዎችን ማቆሸሽ፣.....ቀላል መ/ ሃሜትና ሀሰተኛ ወይም ያልተረጋገጠ ወሬ በሥራ ቦታ መንዛት፣ - ቀላል ሠ/ የሥራ ባልደረባንና የተገልጋይን ስሜት የሚነካ የማይገባ ተግባር መፈጸም፣.....ከባድ ረ/ በቡድን ሥራ ውስጥ የሥራ ባልደረባን ብቃት ማነስ ለቅርብ ኃላፊ ወይም ለሚመለከተው ሌላ ሰው አለመግለጽ፣ .....ቀላል ሰ/ ሥራን ሙያው በሚጠይቀው የሥነ ምግባር ደረጃ አለማከናወን፤.....ከባድ ሸ/ ቢሮን ሳይቆልፉና መብራት ሳያጠፉ መውጣት፣ .....ቀላል አንቀጽ 7. ታማኝነት የባለሥልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. ለሀገራቸው፣ ለህገ መንግስቱና ለኤጀንሲው አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ታማኝና ተገዥ መሆን አለባቸው፡፡ 2. ሥራቸውን በቅርብ ኃላፊ፣ በመ /ቤቱ ኃላፊ በሚሰጡ መመሪያዎች እና በሕግ መሠረት ማከናወን ይኖርባቸዋል፡፡ 3. ኃላፊው ሕገ ወጥ ትእዛዝ እንዲፈጽም ወይም ህጋዊ ለሆነ ጉዳይ የተጠየቀውን መረጃ እንዳይገልጽ በሚያደረግበት ጊዜ ይህንኑ ወዲያውኑ ለመ/ቤቱ ኃላፊ ወይም የሥነ ምግባር መኮንኑ ማሳወቅ አለባቸው፡፡ 4. የመ/ቤቱን ኃብት በጥንቃቄ መያዝና ለተፈቀደው ተግባር ብቻ ማዋል እንዲሁም የሥራ ሰዓትን በማክበር በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋል አለባቸው፡፡ 5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-4) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ በባለስልጣኑ የስራ ሰዓት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪከስራው ጋር የማይገኛኝ ሥራ በቢሮ ውስጥም ሆነ ከቢሮ ውጭ የግል ወይም ሌላ ሰው ስራን ማከናወን /መስራት....ቀላል ለ/ የመመረቂያ ጽሑፎችንና ሌሎች የግል የትምህርት መገልገያዎችን በቢሮ መፃፍ ወይም ማስፃፍ ወይም ማደራጀት ----ቀላል ሐ/ ለግል ሥራ ወይም ሌሎችን ለመርዳት የመ /ቤቱን የጽህፈት መሳሪያዎች ፋክስ፣ ፎቶ ኮፒ መጠቀም .....ቀላል መ/ በመንግስት የፖሊሲ ውሳኔ አሰጣጥ ላይ ጉዳት የሚያደርስ መረጃን ሆን ብሎ መግለጽ ......ከባድ አንቀጽ 8. ግልጽነት የባለሥልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. በተሰጣቸው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት መስራት እና ውሳኔዎችን በግልጽና በወቅቱ መስጠት ይኖርባቸዋል፡፡ የሚሰጧቸው ውሳኔዎች በበቂ ምክንያት የተደገፉ ሊሆኑ ይገባል፡፡ 4 2. የሚሰጧቸው ውሳኔዎች ወይም ትዕዛዞች መመሪያንና ሕግን መቃረን የለበትም፡፡ 3. ለተገልጋይ አገልግሎት ሲሰጡ፣ የመረጃ ጥያቄ ሲቀርብላቸው ግልጽነትን በተላበሰ ሁኔታ መስጠት አለባቸው፡፡ 4. የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ሁሉ ግልጽና ለተገልጋዩ ቀለል ባለ መንገድ መሆን ይኖርበታል፡፡ 5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-4) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ ሕጋዊ ለሆነ ጥያቄ በእጁ የሚገኘውን ምስጢር ያልሆነና ለሕዝብ ግልጽ እንዳይደረግ ያልተከለከለን መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን.....ቀላል ለ/ ለሚያስተላልፈው ውሳኔ ተገቢውን ማብራሪያ ወይም ምክንያት ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን .....ቀላል ሐ/ ለግምገማ የሚያስፈልግ መረጃ አግባብ ባለው አካል ሲጠየቅ በወቅቱ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን .....ቀላል አንቀጽ 9. ምስጢር መጠበቅ የባለሥልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. በባለሥልጣኑ ቆይታቸው ወቅት በሥራ አጋጣሚ ያገኟቸውን ምስጢራዊ መረጃዎችና ሠነዶች በግልጽ ካልተፈቀደ በስተቀር በምስጢር መያዝ ይገባቸዋል፡፡ 2. ባለሥልጣኑን ከለቀቁ በኋላም ቢሆን በሥራቸውና በሙያቸው አጋጣሚ ያወቋቸውንና በምስጢር መያዝ ያለባቸውን መረጃዎች የጊዜ ገደቡ እስከሚያበቃ ድረስ በ ምስጢር መያዝ አለባቸው፡፡ 3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-2) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ ያልተፈቀደን ወይም ምስጢራዊ መረጃን በማናቸውም ሁኔታ ሆነ ብሎ መግለጽ፣......ከባድ ለ/ ያልተፈቀደን ወይም ምስጢራዊ መረጃን በማናቸውም ሁኔታ በቸልተኝነት መግለጽ፣.....ቀላል ሐ/ ምስጢራዊ መረጃን ለግል ጥቅም ማዋል፣ .....ከባድ አንቀጽ 10. ሐቀኝነት የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. በባለስልጣኑ በሚቀጠሩበት ጊዜ የገቡትን ቃል የማክበር፣ በሥራቸው ቅን የመሆን እንዲሁም ከማታለል፣ በተጽእኖ ከመጠቀም እና ከሙስና ነጻ መሆን አለባቸው፡፡ 2. ሐሰተኛ የትምህርት እና የሥራ ልምድ ማስረጃ ማያያዝ /ማቅረብ የለባቸውም፡፡ 3. የመንግስትን የሥራ ጊዜ፣ መገልገያና ኃብት ለግል ጥቅም አለማዋል እና የሥራ መገልገያ ሃብትን በቁጠባ የመጠቀም ግዴታ አለባቸው፡፡ 4. ለሥራ ባልደረባቸው ወይም ለቅርብ ኃላፊያቸው ተጠይቀውም ሆነ ሳይጠየቁ የሚሰጧቸው መረጃዎች እውነት መሆን አለባቸው፡፡ 5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-4) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ በኤጀንሲው አርማና ማህተም ለሕገ ወጥ ድርጊት መጠቀም፣.....ከባድ ለ/ ሃሰተኛ ጥቆማ ማቅረብ፣ .....ቀላል ሐ/ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃና የስራ ልምድ ቅረብ ....ከባድ አንቀጽ 11. ተጠያቂነት የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. ለሚሰጧቸው ውሳኔዎችና ለሚያከናውኗቸው የእለት ተእለት ሥራዎች ለተገልጋዩ ህብረተሰብና ለመ /ቤቱ ተጠያቂነት አለባቸው፡፡ 2. በየጊዜው ለሚያከናውኗቸው ሥራዎችም ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ማቅረብ አለባቸው፡፡ 3. የመንግስትን ፖሊሲና ስትራቴጂ እንዲሁም የኤጀንሲውን ዓላማ የመፈጸምና የማስፈጸም ግዴታ አለባቸው፡፡ 4. ሥራቸውን በአግባቡ ስለመወጣታቸው ምላሽ እንዲሰጡ ተገቢ ጥያቄ ሲቀርብላቸው አስፈላጊውን ማብራሪያ የመስጠት ግዴታ አለባቸው፡፡ 5. ሥራቸውን በወጣው እቅድ መሠረት በወቅቱና በተገቢው ጊዜ ማከናወን አለባቸው፡፡ 5 6. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-5) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ በቢሮ ውስጥ የሚሰራ ሥራ እያለ ተቀምጦ ሥራ አለመስራት፣.....ቀላል ለ/ በሥራ ሰዓት የኮምፕዩተር ጨዋታ መጫዎት ወይም ከሥራ ጋር ባልተያያዘ ሁኔታ ኢነተርኔት ውስጥ ለረዥም ጊዜ በመቆየት የሥራ ጊዜን ማባከን፣ .....ቀላል ሐ/ ሠራተኛው አባል የሆነበት የድርጅት፣ የቦርድ ወይም የሙያ ማህበራት በሚጠሩት ስብሰባ የሥራ ክፍሉን ኃላፊ ሳያስፈቅድ ለመካፈል ሥራ ትቶ መሄድ፣ .....ቀላል መ/ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር ከሥራው ጋር ዝምድና ላላቸው መጠይቆች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን፣.....ቀላል ሠ/ ሆን ብሎ ወይም በግዴለሽነት መረጃዎችን በሥርዓትና በጥንቃቄ አለመያዝ፣.....ቀላል ረ/ ስላከናወናቸው ሥራዎች ለሚመለከተው አካል በወቅቱ የጽሑፍ ወይም የቃል ሪፖርት አለማቅረብ፣ .....ቀላል ሰ/ ስላከናወናቸው ሥራዎች ለሚመለከተው አካል ሆን ብሎ የሚያሳስት ወይም ትክክል ያልሆነ የጽሑፍ ወይም የቃል ሪፖርት ማቅረብ፣.....ከባድ ሸ/ በግዴለሽነት ባህሪ የተዝረከረከ የቢሮ ማኔጅመንት ሥርዓት መከተል፣.....ቀላል አንቀጽ 12. ለሕዝብ ጥቅም መስራት የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. የሚያከናውኗቸው ሥራዎችና የሚሰጧቸው ውሳኔዎች የተገልጋዩን ህብረተሰብና የኤጀንሲውን ጥቅም የሚያስጠብቅ ብቻ መሆን አለበት፡፡ 2. በባለስልጣኑ ሥራ ላይ እያሉ ከመደበኛ ሥራቸው ጋር ሊጋጭ የሚችል ሥራ በመስራት ሊፈጠር የሚችለውን የጥቅም ግጭት ማስወገድ አለባቸው፡፡ 3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-2) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ ከሥራ ጋር ባልተገናኘ ሁኔታ በቤተ መፃህፍት ውስጥ በመቀመጥ የሥራ ጊዜ ማባከን፣ .....ቀላል ለ/ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ከሚያስፈልገው 30 ደቂቃ በላይ ጋዜጣ በማንበብ ብቻ የሥራ ጊዜ ማባከን፣ .....ቀላል ሐ/ በሥራ ሰዓት መስጊድ፣ ቤተ ክርስቲያን ወይም ሱቅና የመሳሰሉ ቦታዎች የቅርብ ኃላፊን ሳያስፈቅዱ መሄድ፣ .....ቀላል መ/ የመ/ቤቱን ተሸከርካሪ ለግል ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አውሎ መገኘት፣.....ከባድ ሠ/ የግልን ጥቅም ከህብረተሰቡ ጥቅም ማስቀደም፡፡ .....ቀላል አንቀጽ 13. ሕጋዊ በሆነ ሥልጣን መገልግል የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. በሕግ ተወስኖ እና በግልጽ ተዘርዝሮ በተሰጠ ኃላፊነት መሰረት የመወሰን ሥልጣን አላቸው፡፡ 2. በሥልጣናቸው ያለአግባብ መገልገል የለባቸውም፡፡ 3. ባላቸው ሥልጣን መሠረት ሲወስኑና መረጃዎችን ሲያጣሩ አግባብ ያለውን ሕግ፣ ደንብና መመሪያ መከተል አለባቸው፡፡ 4. ሥልጣንን መከታ በማድረግ ብቻ በሌሎች ሠራተኞች ላ ይ የሥነ ልቦና ጫና መፍጠር ወይም ማሸማቀቅ የለባቸውም፡፡ 5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-4) የተዘረዘሩትን ግዴታዎችን ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡ - ሀ/ በሥራ ባልደረቦች ወይም በተገልጋዮች ላይ ሥልጣንን ወይም የወሳኝነት ሚናን በማንጸባረቅ ዛቻና ማስፈራራት ተግባር መፈጸም፣ በጥላቻ ኃይለ -ቃል መናገር፣ የጥላቻ ስሜትን ለመግለጽ መገፍተር፣.....ከባድ ለ/ የአሰራር ሥርዓቶችንና ህጎችን በመጣስ መስራት፡፡ .....ከባድ አንቀጽ 14. አለማዳላት የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. በሚሠሯቸው ሥራዎችና በሚሰጧቸው ውሳኔዎች ከአድሎ ነጻ መሆን አለባቸው፡፡ 6 2. አገልግሎትንና ውሳኔን ሲሰጡ በበቂ ምክንያት ተመርኩዞ የጉዳዩን ፍሬ ነገር ከግምት ውስጥ በማስገባት እንዲሁም ውሳኔና አገልግሎት ሲሰጡም በቤተሰብ፣ በጋብቻ፣ በዘር፣ በብሄር/ብሔረሰብ፣ በጾታ፣ በቋንቋ፣ በሀይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት ወይም በሌላ አቋም ያልተመሠረተ መሆን ይኖርበታል፡፡ 3. ሕግን መሰረት በማድረግ ፍትሃዊና ሚዛናዊ ውሳኔ መስጠት አለባቸው፡፡ 4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-3) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ የጉዳዩን ፍሬ ነገር ከግምት ውስጥ ያላስገባና አንድን ግለሰብ ወይም ቡድን ለመጥቀም ሕጋዊ ያልሆነ ምክር መስጠት፣….ቀላል ለ/ በትውውቅ፣ በዘር፣ በብሔር /ብሔረሰብ፣ በጾታ፣ በቋንቋ፣ በሐይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት በመመስረት አድሏዊ ሥራዎችን መፈጸም፡፡.....ከባድ አንቀጽ 15. ሕግን ማክበር የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. ሕገ መንግስቱንና የሀገሪቱን ህጐች የማክበርና የማስከበር እንዲሁም አግባብነት ባላቸው ፖሊሲዎች፣ ሕጐችና ሥልጣን ባለው ኃላፊ በተሰጡ ትዕዛዞች መሠረት ግዴታቸውን መወጣት አለባቸው፡፡ 2. ሕጋዊ የሆኑ ትዕዛዞችን ማክበርና ሌሎች ሠራተኞች ሕጋዊ ትዕዛዞችን እንዲያከብሩ ማበረታታት፣ ከሕግ ውጭ እንዳይሰሩ መምከርና ማገዝ እንዲሁም ከተቀመጡ የአሠራር ሥርዓቶች ውጭ መሆን የለባቸውም፡፡ 3. የደንብ ልብስ መልበስ ግዴታ ያለባቸው ሠራተኞች በሥራ ሰዓት ለሥራ መደቡ የተፈቀደላቸውን የደንብ ልብስ አሟልተውና ንጽህናውን ጠብቀው መልበስ አለባቸው፡፡ 4. የተሰጣቸውን መለያ/ባጅ/ በአግባቡ መጠቀም አለባቸው፡፡ 5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-4) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ በሥራ ሰዓት ያለ በቂ ምክንያት በቢሮ ውስጥ ባለመገኘት ወይም ከቢሮ በመራቅ የሥራ ሰዓትን ማባከን፣ .....ቀላል ለ/ በአንድ ቢሮ ውስጥ ተሰባስቦ ከስራ ጋር ግንኙነት በሌለው አጀንዳ ላይ በማውራት የሥራ ጊዜን ማባከን፣ .....ቀላል ሐ/ በቢሮ እና በስብሰባ ቦታ ሲጋራ ማጨስ .....ቀላል መ/ የመ/ቤቱን ሥራ በተመለከተ ከሥራ ባልደረባ የትብብር ጥያቄዎችንና ተጓዳኝ የሆኑ የበላይ ትዕዛዞችን አለመቀበል፣.....ቀላል ሠ/ የቅርብ የሥራ ኃላፊውን ፈቃድ ሳያገኝ ከሥራ መቅረት ወይም አዘውትሮ ማርፈድ ወይም የሥራ መውጭያ ሳይደርስ ወጥቶ መሄድ.....ቀላል አንቀጽ 16. ለሕዝብ ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ መስጠት የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 1. ደንበኞችን ሙያዊ ሥነ ምግባርን በተላበሰ መልኩ ማስተናገድ አለባቸው፡፡ 2. ደንበኞች ለሚያቀርቡት አገልግሎት በተገቢው የጊዜ ገደብ ምላሽ መስጠት አለባቸው፡፡ 3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-2) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ ተገልጋዮች ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ወቅታዊና ትክክለኛ ምላሽ ለመስጠት ጥረት አለማድረግ፣ .....ቀላል ለ/ ለተገልጋይ ተገቢውን ትህትና አለማሳየትና እገዛ አለማድረግ ወይም መልካም ሥነ ምግባርን በተላበሰ መልኩ አለማስተናገድ፣.....ቀላል ሐ/ ደንበኛ መብቱን በሚመለከት የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲኖር ማድረግ፡.....ቀላል አንቀጽ 17. አርዓያነት የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፡ - 7 1. የመ/ቤቱን ሥራ በሚያከናውኑበት ጊዜ ግንባር ቀደምና ምሳሌ በመሆን የሚጠበቅባቸውን ከፍ ያለ የአርዓያነት ጠባይ በማሳየት በዚህ መመሪያ ውስጥ የተመለከቱትን የሥነ ምግባር መርሆዎች ማጎልበትና በተግባር እንዲተረጎሙ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ አለባቸው፡፡ 2. ኃላፊነት የሚሰማቸው፣ የተሻለ ለውጥን የሚደግፉ፣ የመ/ቤታቸውን መልካም ስም የሚጠብቁና የሥራ ባህል እንዲዳብር የሚተጉ መሆን አለባቸው፡፡ 3. በአመራር ሰጭነት ለሥራ ባልደረቦችና ለህዝብ አርዓያ መሆን፣ የሙያ ብቃትን በማዳበር፣ በቡድን ተቀናጅቶና ተግባብቶ ሥራን በማከናወን አርዓያ መሆን አለባቸው፡፡ 4. ሱስ ከሚያያስይዙ አደንዛዥ እጽ መድኃኒቶች ከመጠቀም፣ ሰክሮ ሥራ ገበታ ላይ ከመገኘት መቆጠብ እንዲሁም የግልና የሥራ አካባቢ ንጽህናን መጠበቅ አለባቸው፡፡ 5. በቅጥር ቀደምተነት ያላቸው ለተከታይ ቅጥር ሠራተኞች የመ/ቤቱን የሕግ ማዕቀፎች (አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች፣ ስለ ሙስና አስከፊ ገጽታዎች እና ስለ ሌሎች መሰል ጉዳዮች እንደአስፈላጊነቱ ግንዛቤ እንዲኖራቸው አስፈላጊ መረጃዎችን በመስጠት፣ ገለጻ በማድረግና በማስረዳት አርዓያ ሆኖ መገኘት አለባቸው፡፡ 6. የሥራ ቦታንና የሥራ መሳሪያን ጽዳትና ንፅህና በመጠበቅ አርዓያ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ 7. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1-6) ሥር የተዘረዘሩትን ግዴታዎች ባለማክበር የሚከተሉትን ጥፋቶች መፈጸም ያስቀጣል፡- ሀ/ ቢሮንና የቢሮ መገልገያዎችን በንጽህናና በሥርዓት አለመያዝ ወይም የጽዳት ጉድለቶች እንዲስተካከሉ አለማድረግ፣ .....ቀላል ለ/ በቢሮ ውስጥ የሚገኙ ፋይሎችንና ማህደሮችን በየጊዜው አለመንከባከብና ከአቧራና ከእርጥበት አለመጠበቅ ወይም እንዲጠበቁ አለማድረግ፣.....ቀላል ሐ/ የባለስልጣኑን አሰራርና የሥነ ምግባር መርሆዎችን እንዲሁም የኤጀንሲውን እሴቶችን ለአዲስ ተቀጣሪ ሠራተኞች አለማሳወቅ፣.....ቀላል መ/ ያለበቂና ህጋዊ ምክንያት ማኛውንም ተገልጋይ በኃይል ከቢሮ ማስወጣት ወይም ለማስወጣት መሞከር፡፡ .....ከባድ ክፍል ሦስት የዲስፕሊን ጥፋቶች የቅጣት አወሳሰን አንቀጽ 18. የዲስፕሊን ቅጣት አይነቶች 1. ቀላል የዲስፕሊን ቅጣቶች ሀ/ የቃል ማስጠንቀቂያ ለ/ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ሐ/ የአንድ ወር የደሞዝ ቅጣት 2. ከባድ የዲስፕሊን ቅጣቶች ሀ/ እስከ ሦስት ወር የሚደርስ የደሞዝ ቅጣት ለ/ እስከ ሁለት ዓመት ድረስ የሚቆይ ከሥራ ደረጃና ደሞዝ ዝቅ ማድረግ ሐ/ ከሥራ ማሰናበት አንቀጽ 19. የዲስፕሊን እርምጃ አወሳሰድ 1. ማንኛውም የዲስፕሊን እርምጃ አወሳሰድ እንዲሁም የቅሬታና የይግባኝ አቀራረብ ሥነ ሥርዓት የሚመራው በፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 515/99 እና በፌደራል መንግስት ሠራተኞች የዲስፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ሥነ ሥርዓት ደንብ ቁጥር 77/94 መሰረት ይሆናል፡፡ 2. በፌደራል መንግስት ሠራተኛች አዋጅ ቁጥር 515/99 እና በዚህ መመሪያ በሁለቱም የሚያስቀጣ ጥፋት የፈጸመ እንደሆነ ጉዳዩ በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ (1) መሰረት ይታያል፡፡ 3. በሥነ ምግባር ግድፈት የተቀጣ ሠራተኛ በፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 515/99 እና በፌደራል መንግስት ሠራተኞች የዲስፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ሥነ ሥርዓት ደንብ ቁጥር 77/94 መሰረት የይግባኝ መብት አለው፡፡ አንቀጽ 20. የዲስፕሊን ቅጣት ዓላማና አፈጻጸም 1. የዲስፕሊን ቅጣት ዓላማው፡ - ሀ/ በሥነ ምግባር የታነጸ ኃላፊና ሠራተኛ ለማፍራት፣ 8 ለ/ ኃላፊዎችም ሆኑ ሠራተኞች የሥነ ምግባር ግድፈት እንዳይፈጽሙ ለማስተማርና ፈጽመው ሲገኙም በማረም ተገቢውን እርምጃ ለመውሰድ፣ የማይታረሙ ሆኖ ሲገኙም ከሥራ ለማሰናበት፡፡ 2. የዲስፕሊን ቅጣት አፈጻጸሙ፡ - ሀ/ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሥራቸውን በአግባቡ ባለመፈጸማቸው ወይም ማድረግ የማይገባቸውን በማድረጋቸው ስለ ጥፋታቸው በፍ/ብሔር ወይም በወንጀል ወይም በሁለቱም ህጎች ተጠያቂነታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ላደረሱት የሥነ ምግባር ግድፈት በዚህ የሥነ ምግባር መመሪያ መሰረት ተገቢው አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰድባቸዋል፣ ለ/ በሥነ ምግባር ግድፈት መነሻነት በዚህ መመሪያ መሰረት የሚሰጡ ውደሳኔዎች ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል፡፡ አንቀጽ 21. የዲስፕሊን ኮሚቴ ሥልጣን የዲስፕሊን ኮሚቴ ሥልጣን በፌደራል መንግሰት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 515/99 እና በፌደራል መንግስት ሠራተኞች የዲስፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ሥነ ሥርዓት ደንብ ቁጥር 77/94 በተሰጠው ሥልጣን መሰረት ይሆናል፡፡ አንቀጽ 22. ስለ ይርጋ 1. ማንኛውም ሠራተኛ የሥነ ምግባር መመሪያውን በመተላለፍ የሥነ ምግባር ግድፈት ከፈጸመ ክሱ የሚቀርብበት በፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 515/99 አንቀጽ 71 ከንኡስ አንቀጽ (1-5) በተገለጸው መሰረት ይሆናል፡፡ 2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ (1) በተመለከተው መሰረት የሚወሰደው የዲስፕሊን እርምጃ የወንጀል ወይም የፍትሐ ብሔር ተጠያቂነትን አያስቀርም፡፡ ክፍል አራት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች አንቀጽ 23. የሥነ ምግባር መኮንኑ ግዴታዎች የባለስልጣኑ የሥነ ምግባር መኮንን ከዚህ የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩታል፤ 1. የፀረ-ሙስና ፖሊሲዎች፣ ሕጎች (ደንቦችና መመሪያዎች)፣ የመልካም ሥነ ምግባር፣ የሙስና አስከፊ ገጽታዎችና ጎጅነት ግንዛቤ እንዲዳብር ያደርጋል፡፡ 2. የፀረ-ሙስና ፖሊሲዎች፣ ሕጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች፣ የኤጀንሲው መመሪያዎችን አፈጻጸም መከበራቸውን ይከታተላል፡፡ 3. ለሙስናና ብልሹ አሰራር ቀዳዳ የሚከፍቱ አሰራሮችን በመፈተሽ ጥናት ማድረግ ወይም ለጥናት መነሻ የሚሆኑ ሀሳቦችን በማመንጨት ለባለስልጣኑ የበላይ ኃላፊ እና ለኮሚሽኑ ያሳውቃል፡፡ 4. ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር በመሆን የአስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ለሕዝብ ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በሚያስችል መልክ እንዲሻሻል እንዲሁም አገልግሎት አሰጣጡ ከአድሎ ነፃ በሆነ መልኩ መከናወኑን ይከታተላል፤ ስለአፈፃፀሙም ለኤጀንሲው የበላይ ኃላፊ ሪፖርት ያቀርባል፡፡ 5. የሥነ ምግባር ጥሰቶችን በሚመለከት በራስ ተነሳሽነት መከታተል እንዲሁም ጥቆማዎች ሲቀርቡ መመዝገብና አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ ሪፖርት ያቀርባል፣ ተፈጻሚነቱንም ይከታተላል፡፡ 6. የሙስና ወንጀልንና ከመልካም ሥነ ምግባር ተቃራኒ የሆኑ ድርጊቶችን በሚያጋልጡ ሠራተኞች ላይ ማናቸውም ተጽእኖ እንዳይደርስ መከታተልና ከተጨባጭ ማስረጃ ጋር ለበላይ ኃላፊ ሪፖርት በማድረግ ተፈጻሚነቱን ይከታተላል፡፡ 7. እንዲሁም ለዚህ መመሪያ አፈጻጸም አግባብነት ያላቸውን ሌሎች ሥራዎች ያከናውናል፡፡ 8. አንቀጽ 24. የመተባበር ግዴታ ማንኛውም የኤጀንሲው ሠራተኛና ኃላፊ ¾ ሥነ ምግባር መኮንኑ ለሥራው የሚፈልገውንና የሚጠይቀውን መረጃና ድጋፍ በመስጠት የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡ አንቀጽ 25. ጥቆማን ስለ ማሳወቅ 1. ማንኛውም የኤጀንሲው ኃላፊ ወይም ሠራተኛ በዚህ መመሪያ ውስጥ የተካተቱ መርሆዎችን የሚፃረር የሥነ ምግባር ጉድለት በማንኛውም መንገድ መፈፀሙን ካወቀ ጉዳዩን ለሥነ ምግባር መከታተያ ክፍል ወይም ለመ /ቤቱ የበላይ ኃላፊ እንዲሁም ጉዳዩ ከበድ ያለ ከሆነም ለኮሚሽኑ ማሳወቅ አለበት፡፡ 9 2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሰረት የሚቀርበው ጥቆማ እውነተኛ፣ ከበቀል የፀዳና ምክንያታዊ በሆነ እምነት ላይ የተመሰረተ መሆን ይኖርበታል፡፡ 3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሰረት ጥቆማ አቅራቢው ከማናቸውም የበቀል ጥቃት የመጠበቅ መብት አለው፡፡ 4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሰረት ጥቆማ አቅራቢው ማንነቱ እንዳይገለጽ ከፈለገ ማንነቱ ምስጢራዊ መያዝ አለበት፡፡ አንቀጽ 26. ስለ ቀረቡ ጥቆማዎች አፈጻጸም 1. በኤጀንሲው ስለተፈጸሙና ሊፈጸሙ ስለታቀዱ የሙስና ወንጀሎችና ብልሹ አሰራሮች አንዲሁም የሥነ ምግባር መርሆዎች ጥሰትን የተመለከተ፣ ያወቀ ማንኛውም የኤጀንሲው ሠራተኛ ጥቆማውን ለኤጀንሲው የሥነ ምግባር መኮንኑ በቃል፣ በጽሁፍ፣ በስልክ ወይም በሌሎች ማናቸውም መንገዶች ቢቻል ከደጋፊ ማስረጃ ጋር ማቅረብ ይችላል፡፡ 2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሰረት በቀረበው ጥቆማ መሰረት የኤጀንሲው የሥነ ምግባር መኮንን ጥቆማ ወደተደረገበት ክፍል በመሄድ መረጃዎች ይሰበሰባሉ፣ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት የተገኘው ግኝት ከመፍትሔ ሃሳብ ጋር ለኤጀንሲው የበላይ ኃላፊ ይቀርባል፡፡ 3. ስለተወሰደው እርምጃ አፈጻጸም ክትትል ይደረጋል፣ ሪፖርትም ይቀርባል፡፡ አንቀጽ 27. ተፈጻሚነት ስለ ማይኖራቸው ሕጎች ከዚህ መመሪያ ጋር የሚቃረን ማንኛውም መመሪያ ወይም የአሰራር ልምድ በዚህ መመሪያ የተሸፈኑ ጉዳዮችን በሚመለከት ብቻ ተፈጻሚነት አይኖራቸውም፡፡ አንቀጽ 28. መመሪያውን ስለማሻሻል ይህ መመሪያ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በማናቸውም ጊዜ ሊሻሻል ይችላል፡፡ አንቀጽ 29. መመሪያው የሚጸናበት ጊዜ ይህ የሥነ ምግባር መመሪያ ከጥቅምት 1 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚነት ይኖረዋል፡፡
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
499
ትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን ተሻሽሎ የወጣ አዋጅ፡፡ መንግስት የያዘዉን የእድገት መንገድና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ቀጣይነት እንዲኖረው ሙስና እና ብልሹ አሰራር የማይሸከምና በብቃት ለመዋጋት ዝግጁ የሆነ ህብረተሰብ ለመፍጠር ልዩ ትኩረት መስጠት የሚያስፈልግ መሆኑ ስለታመነበት፣ የተሻሻለው የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ማቋቋምያ አዋጅ ቁጥር 208/2003 ዓ.ም በምርመራ፣በክስና መረጃ በማሰባሰብ ግልፅ በማድረግ ማሻሻልና አዳዲስ ድንጋጌዎች እንዲካተቱ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በህዝባዊ ድርጅቶች ዉስጥ የሙስና ወንጀል እንዳይፈፀም መከላከልና መቆጣጠር የሙስና ወንጀሎች ሲፈፀሙም የመመርመርና የመክሰስ ስልጣን ለኮሚሽኑ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ተሻሽሎ በወጣዉ የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ህገ መንግስት ዓንቀፅ 49/3/ሀ/ መሰረት ይህ አዋጅ አዉጥቷል፡፡ ክፍል አንድ ጠቅላላ አንቀፅ 1∙አጭር ርእስ፡ ይህ ኣዋጅ “የትግራይ የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣ አዋጅ ”ተብሎ ይጠቀሳል፡፡ አንቀፅ 2.ትርጉም፡ 1. ‘‘ኮሚሽን‘‘ ማለት የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ነው፣ 2. ‘‘ኮሚሽነርና ምክትል ኮሚሽነር‘‘ ማለት እንደ ቅደም ተከተሉ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር እና ምክትል ኮሚሽነር ነው፣ 3. ‘‘ሰው‘‘ ማለት የተፈጥሮ ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው ነው፣ 4. ‘‘የመንግስት መስርያ ቤት‘‘ ማለት የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በህግ ያቋቋመውና በሙሉ ወይም በከፊል በጀት የሚመድብለት ነው፣ 5. ‘‘የመንግስት የልማት ድርጅት‘‘ማለት የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሙሉ ወይም በከፊል በጀት የሚመደብለት የልማት ድርጅት ወይም አክስዮን ማሕበር ነው፣ 6. ‘‘የመንግስት ባለ ስልጣናት” ማለት ርዕሰ መስተዳድርና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የርዕሰ መስተዳድሩ አማካሪዎች፣ ኣፈ- ጉባኤና ምክትል አፈ-ጉባኤ፣የክልል አፈ ጉባኤ አማካሪዎች ፣ የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና ምክትል፣ቢሮ ሃላፊዎችና ምክትል ቢሮ ሃላፊዎች፣የጠቅላይ ፍ/ቤት ኘረዚደንትና ምክትል ኘረዚደንት፣ የከፍተኛ ፍርድቤት ዳኞችና ሬጅስትራሮች፣ ኮሚሽነርና ምክትል ኮሚሽነር፣የኤጀንሲ ሃላፊና ምክትል ሃላፊ፣ ዋና ኦዲተርና ምክትል ዋና ኦዲተር፣ የፅሕፈት ቤት ሓላፊና ምክትል ሃላፊ፣ የኢንተርኘራይዝ ሃላፊና ምክትል ሃላፊ፣ የኢንስቲዩቲት ሃላፊና ምክትል ሃላፊ፣ የመንግስት መስርያ ቤት ዋና ዳይሬክተርና ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣የመንግስት የልማት ድርጅት ሃላፊና ምክትል ሃላፊ፣በተመሳሳይ ደረጃ የሚገኙ ባለስልጣኖች፣ የዞን ዋና አስተዳዳሪ እና ምክትል ዋና አስተዳደሪ፣ የዞን የዋና አስተዳዳሪ አማካሪና የፅሕፈት ቤት ሃላፊ፣የከፍተኛና የወረዳ ፍ/ቤት ኘረዚደንቶችና በነዚህ ደረጃዎች የሚገኙ ዳኞችና ረጂስትራር እንዲሁም በዞን ደረጃ የሚገኙ የመስርያ ቤት ሃላፊዎች ያጠቃልላል፣ የከተማ ከንቲባና ምክትል ከንቲባ፣ የከተማ ከንቲባ አማካሪ፣የማዘጋጃ ቤት ስራ አስከያጅ፣ የፅሕፈት ቤት ሓላፊ፣ የወረዳ፣የከተማና ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ኣፈ-ጉባኤና ምክትል ኣፈ-ጉባኤ፣የወረዳና ክፍለ ከተማ ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና ምክትል ሰብሳቢ፣የወረዳና ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳደሪና ምክትል ዋና አስተዳዳሪ፣የወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ኣማካሪ፣የወረዳና የክፍለ ከተማ ፅሕፈት ቤትና ምክትል ሓላፊ በተመሳሳይ ደረጃ የሚገኙ የወረዳ ባለስልጣናት ያጠቃልላል፣ 7. ‘‘የመንግስት ሰራተኛ‘‘ ማለት በዚህ አንቀፅ ንኡስ አንቀፅ 6 ውስጥ ከተጠቀሱት ውጭ በክልሉ የመንግስት መስርያ ቤት ወይም የልማት ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ፣ ተሽሞ፣ተመድቦ ወይም በህዝብ ተመርጦ የሚሰራ የተፈጥሮ ሰው ነው፣ 8. ”ህዝባዊ ድርጅት” ማለት በማንኛዉም አግባብ ከአባላት ወይም ከህዝብ የተሰበሰበ ወይም ለህዝባዊ አገልግሎት ታስቦ የተሰበሰበ ገንዘብ፣ንብረት ወይም ሌላ ሃብት የሚያስተዳድር አካልና አግባብነት ያለዉ ኩባንያን የሚያካትት የግል ዘርፍ ሲሆን፣ የሚከተሉትን አያካትትም፦ ሀ) የሃይማኖት ድርጅትን ለ) የፖለቲካ ድርጅት (ፓርቲ) ሐ) የአለም አቀፍ ድርጅትን እና መ) ዕድርና ተመሳሳይ ባህላዊ ወይም ሃይማኖታዊ ይዘት ያለዉ ማሕበርን 9. ‘‘የህዝባዊ ድርጅት ባለስልጣናት‘‘ማለት የድርጅት መሪ ወይም ሃላፊ ወይም ስራ አስፈፃሚ ወይም ስራ አስኪያጅ፣የቦርድ ሃላፊ፣የዳይረክተሮች ቦርድ አባል፣የክፍል ሃልፊ ወይም የስራ ሂደት ሃላፊ፣የአክስዮን ማህበር ወይም የበጎ አድራጎት ድርጅት የሚያደራጅ ሰዉ ሆኖ የኮሚቴ አባል ያካትታል፣ 10. ”የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ” ማለት በዚህ አንቀፅ ንኡስ ዐንቀፅ 9 ከተጠቀሱት ውጪ በህዝባዊ ድርጅት ዉስጥ ተቀጥሮ፣ተመድቦ ወይም በአባላት ተመርጦ በቋሚነት ወይም በጊዚያዊነት የሚሰራ የተፈጥሮ ሰው ነው፡፡ 11.‘‘የሙስና ወንጀል‘‘ማለት የሙስና ወንጀል ለመደንገግ በወጣው የፌደራል አዋጅ ቁጥር 881/2007ዓ.ም የተደነገጉት የሙስና ወንጀሎች ናቸው፣ 12. ‘‘ከባድ የስነ ምግባር ጥሰት‘‘ ማለት በክልሉ የመንግስት ሰራተኞች የስነ ምግባር ደንብ እና በኮሚሽኑ የአላማ ፈፃሚ ሰራተኞች መተዳደርያ ደንብ መሰረት ከስራ ሊያሰናብት የሚችል ጥፋት ነው፣ 13. ‘‘ከባድ የሙስና ወንጀል‘‘ ማለት ሀ/ ከፍተኛ ስትራቴጅያዊ ጠቀሜታ ባላቸው የመንግስት መስርያ ቤቶች፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶችና ህዝባዊ ድርጅቶች የሚፈፀሙ ከ100‚000 ብር በላይ የገንዘብ መጠን ያላቸዉ የሙስና ወንጀሎች ወይም፣ ለ/በክልሉ የመንግስትና ህዝባዊ ድርጅቶች ባለስልጣናት የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች ወይም፣ ሐ/በክልሉ ኢኮኖሚ፣ ሰላምና ፀጥታ እንዲሁም በህብረተሰቡ ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሱ ወይም ሊያደርሱ የሚችሉ የሙሱና ወንጀሎች ናቸው፣ 14. ‘‘የባንክ ሂሳብ‘‘ ማለት በባንክ እንዲሁም በፋይናንስ ተቋማት የተቀመጠ ገንዘብ፣ ወርቅና ሌሎች ውድ ዋጋ ያላቸዉ እቃዎች እንዲሁም አንድ ደንበኛ ከባንኩ ጋር የሚያደርጋቸው ማናቸውንም የሃብት ግንኙነቶች ወይም ልውውጥ የሚያጠቃልል ነው፣ 15. "አዋጅ" ማለት የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የስነ- ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን እና አዋጅ ቁጥር 271/2008ዓ.ም ለማሻሻል የወጣ ነዉ፣ ገፅ 5 ነጋሪት ጋዜጣ ትግራይ ቁ. ኣዋጅ 271/2008 ዓ.ም ገፅ 5 የትግራይ ነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ቁ. 271/2008ዓ.ም 6 16.”ጠቋሚ” ማለት ተፈፂሙ ወይ ክፍፀም እዩ ኢሉ ዝኣመኖ ገበን ግዕዝይና ዝምልከት ሓበሬታ ኣግባብ ንዘለዎ ኣካል ወይ ንኻልእ ፍትሒ ኣካል፣ ንመንግስታዊ ቤት ዕዮ ፣ንትካል ልምዓት መንግስቲ ወይ ንህዝባዊ ትካል ወይ ንላዕለዋይ ሓላፊ ህዝባዊ ትካል ወይ ብሕጊ ወይ ብመምርሒ ገበን ግዕዝይና ጥቆማ ክቕበል ሓላፍነት ንዝተዉሃቦ ካልእ ኣካል ዘቕርብ ሰብ እንትኸዉን ነዞም ዝተጠቐሱ ኣካላት ጥቆማ እንተዘየቕረበ’ዉን ገበን ግዕዝይና ዝተፈፀመሉ ዋኒን ኦዲት ዝገብር ወይ ኣብ ኦዲት ተግባሩ ዝተፈፀመ ግዕዝይና ዘቃለዐ ኦዲተርን ጥቆማ ዘፃሪ ወይ ዝምርምር ሰብ የካትት፣ 17.‘‘ክፍሊ ክትትል ስነ-ምግባር‘‘ ማለት ግዕዝይናን ብልሽው ኣሰራርሓን ንምክልኻልን ንምቁፅፃርን ተግባራት ፅቡቕ ስነ-ምግባር ንምስፍሕፋሕ ዝሰርሕ ኣብ ሕድሕድ ቤት ዕዮ መንግስቲ፣ ትካል ልምዓት መንግስትን ህዝባዊ ትካልን ዘሎ ማሓውር እዩ፣ 18.‘‘ኣግባብነት ዘለዎም ኣካላት‘‘ ማለት መንግስታዊ ኣብያተ ዕዮ፣ ትካላት ልምዓት መንግስትን ህዝባዊ ትካላትን እዮም፣ 19.‘‘ኣግባብነት ዘለዎ ኩባንያ‘‘ ማለት ብህዝባዊ ትካል ዝተጣየሸ ሓላፍነቱ ዝተወሰነ ኩባንያ እንትኸውን እዚ ዓይነት ኩባንያ ምስ ካልኦት ዘጣይሾ ማሕበር ሽርክና ዘጠቓልል እዩ፡፡ 16. ”ጠቋሚ” ማለት ተፈፅመዋል ወይም ሊፈፀም ነዉ ብሎ ያመነዉን የሙስና ወንጀል የሚመለከት መረጃ አግባብ ላለዉ አካል ወይም ለሌላ የፍትህ አካል፣ ለመንግስት መስርያ ቤት፣ለመንግስት የልማት ድርጅት ወይም ለህዝባዊ ድርጅት ወይም ለህዝባዊ ድርጅት የበላይ ሃላፊ ወይም በህግ ወይም በመመሪያ የሙስና ወንጀል ጥቆማን እንዲቀበል ሃላፊነት ለተሰጠዉ ሌላ አካል የሚያቀርብ ሰዉ ሲሆን ለእነዚህ ለተጠቀሱት አካላት ጥቆማ ባያቀርብም የሙስና ወንጀል የተፈፀመበትን ጉዳይ ኦዲት የሚያደርግ ወይም በኦዲት ከተደረገ በኃላ ሙስና መፈፀሙን ያጋለጠ ኦዲተር እና ጥቆማን የሚያጣራ ወይም የሚመረምር ሰዉን ያካትታል፣ 17. ‘‘የስነ ምግባር ክትትል ክፍል” ማለት ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ፣መልካም ስነ ምግባር ለማስፋፋት የሚሰራ በእያንዳንዱ የመንግስት መስርያ ቤት፣ የመንግስት የልማት ድርጅትና ህዝባዊ ድርጅት ያለ መዋቅር ነው፣ 18. ‘‘አግባብነት ያላቸው አካላት‘‘ ማለት የመንግስት መስርያ ቤቶች ፣የመንግስት የልማት ድርጅቶችና ህዝባዊ ድርጅቶች ናቸው፣ 19. ‘‘አግባብነት ያለው ኩባንያ‘‘ ማለት በህዝባዊ ድርጅት የተቋቋመ ሃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ሲሆን እንደዚህ ዓይነት ኩባንያ ከሌሎች ጋር የሚያቋቁመውን የሽርክና ማህበር የሚያጠቃልል ነው፡፡ ገፅ 6 ነጋሪት ጋዜጣ ትግራይ ቁ.ኣዋጅ 271/2008 ዓ.ም ገፅ 6 የትግራይ ነጋሪት ጋዜጣ አ”ጠቋሚ” ማለት ተፈፅመዋል ወይም ሊፈፀም ነዉ ብሎ ያመነዉን የሙስና ወንጀል የሚመለከት መረጃ አግባብ ላለዉ አካል ወይም ለሌላ የፍትህ አካል፣ ለመንግስት መስርያ ቤት፣ለመንግስት የልማት ድርጅት ወይም ለህዝባዊ ድርጅት ወይም ለህዝባዊ ድርጅት የበላይ ሃላፊ ወይም በህግ ወይም በመመሪያ የሙስና ወንጀል ጥቆማን እንዲቀበል ሃላፊነት ለተሰጠዉ ሌላ አካል የሚያቀርብ ሰዉ ሲሆን ለእነዚህ ለተጠቀሱት አካላት ጥቆማ ባያቀርብም የሙስና ወንጀል የተፈፀመበትን ጉዳይ ኦዲት የሚያደርግ ወይም በኦዲት ከተደረገ በኃላ ሙስና መፈፀሙን ያጋለጠ ኦዲተር እና ጥቆማን የሚያጣራ ወይም የሚመረምር ሰዉን ያካትታል፣ 17. ‘‘የስነ ምግባር ክትትል ክፍል” ማለት ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ፣መልካም ስነ ምግባር ለማስፋፋት የሚሰራ በእያንዳንዱ የመንግስት መስርያ ቤት፣ የመንግስት የልማት ድርጅትና ህዝባዊ ድርጅት ያለ መዋቅር ነው፣ 18. ‘‘አግባብነት ያላቸው አካላት‘‘ ማለት የመንግስት መስርያ ቤቶች ፣የመንግስት የልማት ድርጅቶችና ህዝባዊ ድርጅቶች ናቸው፣ 19. ‘‘አግባብነት ያለው ኩባንያ‘‘ ማለት በህዝባዊ ድርጅት የተቋቋመ ሃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ሲሆን እንደዚህ ዓይነት ኩባንያ ከሌሎች ጋር የሚያቋቁመውን የሽርክና ማህበር የሚያጠቃልል ነው፡፡ አንቀፅ 3.የፆታ አገላለፅ፡ በዚህ አዋጅ በወንድ ፆታ የተገለፀዉ ሁሉ ለሴት ፆታም የሚያካትት ነዉ፡፡ አንቀፅ 4.የኮሚሽኑ ዓላማዎች፡ 1. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ትምህርት በማስፋፋት የነቃ እና ሙሱናን የማይሸከም ሕብረተሰብ እንዲፈጠር ጥረት ማድረግ፣ 2. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የሙሰና ወንጀል እና ብልሹ አሰራርን መከላከል፣ 3. የሙስና ወንጀል እና ብልሹ አሰራርን መከታተል፣መመርመርና መክሰስ። ክፍል ሁለት ስለኮሚሽኑ መቋቋም ፣አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር አንቀፅ 5. የኮሚሽኑ መቋቋም፡ 1. የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የስነ- ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሸን እንደገና በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል፣ 2. የኮሚሽኑ ተጠሪነት ለትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ይሆናል። አንቀፅ 6.አደረጃጀት ኮሚሽኑ፣ 1. በርዕሰ መስተዳድሩ የሚሾሙ ኮሚሽነርና ምክትል ኮሚሽነር፣ 2. ስራውን ለመፈፀም የሚያስፈልጉት ሌሎች ሰራተኞች ይኖሩታል። አንቀፅ 7.ስለ ኮሚሽኑ የሥራ ነፃነት በዚህ አዋጅ ኣንቀፅ 5 ንኡስ አንቀፅ 2 የተደነገገው ቢኖርም ኮሚሽኑ በሚመረምራቸው፣ክስ በሚመሰርትባቸው ወይም ክሰ በመሰረተባቸው ጉዳዮች ላይ ከማንኛውም ፈፃሚ አካልና ሌሎች አካላት ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ነፃ ሆኖ በህግ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ይሰራል። አንቀፅ 8.ዋና ፅሕፈት ቤት የኮሚሽኑ ዋና መስርያ ቤት መቐለ ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በዞንና ወረዳ ቅርንጫፍ ፅሕፈት ቤት ሊኖረው ይችላል። አንቀፅ 9.የኮሚሽኑ ስልጣንና ተግባር በሌሎች ህጎች ለኮሚሽኑ የተሰጠዉ ስልጣንና ተግባር እንደተጠበቀ ሆኖ፡ 1. የሰራተኞቹ ሞያዊ ብቃትና ስነ-ምግባር ለማሳደግ የአቅም ግንባታ ስራዎች ያካሄዳል፣ 2. ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ስለሙስና እና ጎጂነቱ ህዝቡ እንዲረዳ እና አስተሳሰቡ እንዲጎለብት ማስተማር፣ በህዝብ አገልግሎት እና በህብረተሰብ ውስጥ መልካም ስነ-ምግባር ማስፋፋት፣ ሙስናን እና ብልሹ አሰራርን መዋጋትና ማስተባበር፣ 3. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር በመንግስት መስርያ ቤቶች፣ በመንግስት የልማትና ህዝባዊ ድርጅቶች ውስጥ ለሙስና እና ብልሹ አሰራርየተጋለጡና ሊጋለጡ የሚችሉ የአሰራር ሰርዓቶች በማጥናት ወይም እንዲጠኑ በማድረግ እንዲሻሻሉ ማማከርና ማሳሰብ፣የአሰራር ስርዓቶቹ የተሻሻሉ መሆናቸውን መከታተል እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ተገቢ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድ ወይም ውሳኔ እንዲሰጥ አግባብ ላለው አካል በማሳወቅ ወይም በማሳሰብ ሙሱናን የመከላከል፣ በሌሎች ሰዎች ወይም ኣካላት ሲጠየቅ ተመሳሳይ ምክርና ድጋፍ መስጠት፣ 4. ከምርመራና ተገቢ እርምጃ ከመዉሰድ ጋር የተያያዘ፣ ሀ)በመንግስት መስርያ ቤቶች፣በመንግስት የልማትና ህዝባዊ ድርጅቶች ዉስጥ ከባድ የስነ- ምግባር ጥሰት ስለመፈፀሙ ጥቆማ ሲደርሰዉ ወይም በቂ ጥርጣሬ ሲኖረዉ ያጣራል ወይም እንዲጣራና ተገቢዉ እርምጃ እንዲወሰድ ይከታተላል፣ ለ)ከምርመርና ክስ ጋር የተያያዘ፡ 1. በመንግስት መስርያ ቤቶች፣በመንግስት የልማት ድርጅቶች ወይም በህዝባዊ ድርጅቶች ውስጥ በሙስና ወንጀሎች አዋጅና በሌሎች ሕጎች የተመለከቱት የመስና ወንጀሎች በመንግስት መስርያ ቤቶች፣ በልማት ድርጅቶች ወይም በህዝባዊ ድርጅቶች ባለስልጣናት ወይም ሠራተኞች ወይም በሌሎች ሰዎች ስለመፈፀማቸው ወይም፣ 2. በዚህ አዋጅ አንቀፅ 22 እና በአዋጅ ቁጥር 434/1997 ዓ.ም የተደነገጉ ወንጀሎች ፣ ከኮሚሽኑ ሥልጣንና ተግባር ኣንፃር የሙስና ወንጀል ምርመራ፣ ክስና የፍርድ ሂደትን ከማደናቀፍ ጋር የተያያዙ ወንጀሎች እና በሌሎች ህጎች የተደነገጉ ወንጀሎች በማንኛውም ሰው ስለ መፈፀማቸው መረጃ ሲደርሰዉ ወይም በቂ ጥርጣሬ ሲኖረዉ ያጣራል፣ክስ ይመሰርታል ወይም እንዲመረመርና እንዲከሰስ ያደርጋል። 5. በዚህ አንቀፅ ንኡስ አንቀፅ 4 የተገለፀው ቢኖርም፡ ሀ/ ሌላ ወንጀል ከሙስና ወንጀል ጋር ተጣምሮ ተፈፅሞ ሲገኝ ኮሚሽኑ ለሁለቱም የወንጀል ተግባሮች ይመረምራል ፣ይከሳል ለ/የሙስና ወንጀል ተብሎ ክስ የተመሰረተበት ድርጊት በክርክር ሂደት የሙሰና ወንጀል ሆኖ ባይገኝም የክሱ ክርክር የመቀጠል ስልጣን አለው፣ 6. በዚህ አዋጅ ድንጋጌ አንቀፅ 10 ና 11 የተገለፀው ውክልና የመስጠት ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ፦ ሀ/ ኮሚሽኑ በፖሊስ የወንጀል ምርመራ መሰረት በማድረግ የሚገኙ ወይም ክስ የተመሰረተባቸው የሙስና ወንጀሎች በወንጀሉ የተገኘ ጥቅም ከተመለሰ በኃላ በድርድር እንዲያልቁ ማድረግ ይችላል። የሙስና ወንጅሎች በድርድር ስለሚጠናቀቅበት ሁኔታ በሚወጣ ደንብ ይወሰናል፣ 7. በሙስና ወንጀል የማጣራት ሂዲት በተሻሻለው የፀረ-ሙስና ልዩ የማስረጃ ስነ ስርዓት ሕግና የወንጀል ሕግ ስነ ስርዓት መሰረት ማናቸውም ቅጥር ግቢ፣ የስራ ቦታ፣ ተሽከርካሪ ወይም ሌላ ንብረት እንደየ አስፈላጊነቱ የመፈተሽ የመበርበርና የመያዝ፣ 8. ከሙስና ወንጀል ጋር በተያዘ በባንክ እንዲሁም በፋይናንስ ተቋማት የተቀመጠ ገንዘብ ለመኖሩ በቂ ጥርጣሬ ወይም መረጃ ሲኖረው በማናቸውም ባንክ እንዲሁም በፋይናንስ ተቋማት የሚገኝ የተጠርጣሪዎች የባንክ ሂሳብ በኮሚሽነሩ ትእዛዝ እንዲመረመር የማድረግ፣ መረጃ የማግኘት እናአስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በፍርድ ቤት ትእዛዝ እንዲታገድ የማድረግ፣ 9. በህግና ኣሰራር መሰረት ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ በኮሚሽነሩ ፊርማ የመጠየቅ፣ 10. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር በህግ መሰረት ሃብታቸውንና የገንዘብ ጥቅማቸውን እንዲያስመዘግቡ ግዴታ ያለባቸው ባለስልጣናትና ሰራተኞች መዝግቦ መያዝ ወይም ተመዝግቦ እንዲያዝ የማድረግ፣ 11. ሃብትና ገንዘባቸው ያላስመዘገቡ የክልሉ ባለስልጣናት እና ሰራተኞች የሚመለከት ጥቆማ ለሚያቀርቡ አካላት በህግ መሰረት ማግኘት የሚገባቸውን ጥቅም ማግኘታቸው ያረጋግጣል፣ ይከታተላል፣ 12. ለህግ አውጪውና የዳኝነት አካላትን ሳይጨምር ለመንግስት መስርያ ቤቶች፣ ለመንግስት የልማት ድርጅቶችና ለህዝባዊ ድርጅቶች የሚያገለግሉ የስነ ምግባር ደንቦች መዘጋጀታቸው ማረጋገጥ፣ እንዲዘጋጁ ማድረግ፣ በተግባር መዋላቸውን መከታተል፣ ከህግ አውጪው እና ከዳኝነት አካላት ጥያቄ ሲቀርብለት በስነ ምግባር ደንብ አዘገጃጀት ረገድ ምክር ይሰጣል፣ 13. የፀረ ሙስና ሕጎችና የስነ ምግባር ደንቦች በተግባር ላይ መዋላቸውን መከታተል ለአፈፃፀማቸው ጠቃሚ ምክር መስጠት፣በምርመራና ክስ የሚገኙ የሙስና ወንጀሎችና በፍርድ ሂደት ያለ የሙስና ወንጀል ክስ በሕግ መሰረት ለህዝብ ጥቅም ማንሳት፣ ዝርዝር አፈፃፀሙ በሚወጣ በደንብ ይወሰናል፣ 15. በወንጀሉ የተገኘ ጥቅም እንዲመለስ በማድረግ በሙስና ወንጀል ክስ የተመሠረተባቸው ወይም በምርምራ ሂደት ላይ ያሉ የሙስና ወንጀሎች በማቋረጥ እንዲቋጩ ማድረግ፣ ዝርዝር አፈፃፀሙ በሚወጣ ደንብ ይወሰናል፣ 16. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር ሙስናንና ስነ ምግባር በተመለከተ ጥናትና ምርምር ማድረግ፣ ተመሳሳይ ስራ ለሚሰሩ ኣካላት መደገፍ፣ የኮሚሸኑን ዓላማዎች ለማራመድ የሚረዱ ሪፖርቶች እና ቴክኒካዊ ጥናቶችን አሳትሞ ያሰራጫል፣ 17. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር ለሙስና ወንጀል ጠቋሚዎችና ምስክሮች የአካል እና የሥራ ዋስትና ጥበቃ የሚሰጥበትን ሁኔታ ማመቻቸት፣ በህግ መሰረት ጥበቃ የማድረግ፣ 18. ሙስናን በመታገልና በመከላከል ረገድ ጥሩ ውጤት ያስገኙ ሰዎችን ፣ መሥርያ ቤቶችን እና ድርጅቶችን አወዳድሮ ለሽልማት የሚበቁበት ሥርዓትና መሊኪያ መዘርጋትናተግባራዊ ማድረግ፣ 19. ተመሳሳይ ዓላማ ካላቸው የፌደራልና የክልል አካላት ጋር ግንኝነትና የሥራ ትብብር ይፈጥራል፣20. አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የሥነ-ምግባር ክትትል ክፍሎች እንዲቋቋሙ ድጋፍ መስጠት፣ ለዚህ ዓላማ የሚያስፈልጉ የተለያዩ የፀረ-ሙሰና አደረጃጀቶች እንዲቋቋሙ የማድረግ፣ 21. ከህዝብ መረጃ የሚያገኝበትና ለህዝብ መረጃ የሚሰጥበት ዘዴዎችን ይቀይሳል፣ ያስፈፅማል፣ 22. በህግ ወይም ብፍርድ ቤት ትእዛዝ ካልሆነ በስተቀር ከሙስና ወንጀል ጋር የተያያዙ ጥቆማዎችና ምስክርነት በሚስጢር ይይዛል። አንቀፅ 10.በሙስና ወንጀል ምርመራ ውክልና ሰለመስጠት 1. ኮሚሽኑ በዚህ አዋጅ አንቀፅ 9 ንኡስ አንቀፅ 4 ከተሰጠዉ ከባድ የሙስና ወንጀል ውጪ ከባድ ያልሆነ የሙስና ወንጀል የመመርመር ውክልና በሙሉ ወይም በከፊል እንደሁኔታው ለትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ አካላት ሊሰጥ ይችላል፣ 2. በየደረጃው ያሉ የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ አካላት በዚህ አንቀፅ ንኡስ አንቀፅ 1 መሰረት ውክልና ባይሰጣቸውም በዚህ አዋጅ አንቀፅ 9/4/ መሰረት በኮሚሽኑ የስልጣን ክልል የሚወድቅ የሙስና ወንጀል ለመፈፀሙ ጥቆማ ሲደርሳቸው ወይም በቂ ጥርጣሬ ሲኖራቸው ምርመራ መጀመር ይኖርባቸዋል፣ሆኖም ስለተጀመረው ምርመራ በ24 ሰዓት ዉስጥ ለኮሚሽን ማሳወቅ አለባቸው
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]
500
በሙስና ዙሪያ የተጠኑ ጥናቶች ሥራ ላይ አለመዋላቸው ተገለጸ፡፡ ባሕር ዳር፡ ሰኔ 9/2011ዓ.ም (አብመድ) የፌዴራል ሥነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በተመረጡ ዘርፎች ላይ ጥናት ቢያስጠናም የጥናቱን ውጤት ተቀብሎ የሚተገብር ተቋም እንደሌለ አስታወቀ። ኮሚሽኑ ትናንት በአዳማ ከተማ ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች እና አባላት በሰጠው ስልጠና ላይ እንዳስታወቀው የሙስና እንቅስቃሴና ስጋት በሚታይባቸው ዘርፎች ላይ የተካሄደውን የጥናት ውጤት የተገበረ አካል የለም። በኮሚሽኑ የሥነ ምግባር አውታሮች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ሀረጎት አብርሃ እንዳሉት ኮሚሽኑ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሠረት በተለያዩ ጊዜያት የሙስና ስጋት እና እንቅስቃሴ በሚታይባቸው እንደ መሬት፣ ገቢዎች እና መሠል ሴክተር መሥሪያ ቤቶች እንዲጠኑ ተደርጎ ምክረ ሐሳብ ቢቀመጥም ጥናቱን እንደ ግብዓት ተጠቅሞ ችግሮችን ለማሻሻል የሚጠቀም ተጠኚ መስሪያ ቤትም ሆነ የበላይ አካል የለም። ዳይሬክተሩ እንዳሉት ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ እና አባላት የተዘጋጀው ስልጠናም ኮሚሽኑ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክን ጨምሮ ከሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች እና አካላት ጋር ጥምረት በመፍጠር የተጠኑ ጥናቶችን እንዲተገበሩ ለማድረግ ነው፡፡ እንደ አቶ ሀረጎት ገለጻ የስልጠናው መድረክ ለኮሚሽኑ ግብዓት እንደሚሆንና ይህም የአዲስ አበባን ምክር ቤት በሙስና ትግሉ ላይ ሚናውን ከፍ ለማድረግ ይረዳል፡፡ ‹‹በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሚገኙ የሥነ ምግባር መኮንኖች እንደጠላት እየተቆጠሩ ቢሮ እንኳን የሌላቸው ባለሙያዎች አሉ፤ እነዚህንም ባለሙያዎች ወደ ሥራቸው እንዲገቡና እንቅፋት እንዳይገጥማቸው የምክር ቤቱ አባላት ይረዱናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን›› ብለዋል። ጠንካራ አገር ለመገንባትም ሙስናን መከላከል ወሳኝ በመሆኑ ሰፊ ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው የተናገሩት ዳይሬክተሩ በዚህ ወቅት መንግሥት ጠንካራ አቋም ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሆነ ገልጸዋል። የአ.ፕ.ድ እንደዘገበው በአገሪቱ ስር የሰደደውን የሙስና ችግር ለማስወገድ የተሻለ የፀረ-ሙስና ትግል ለማድረግ በዚህ ወቅት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል። የፌዴራል ሥነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ አትክልቲ ግደይ ደግሞ ጊዜ እና ገንዘብ የፈሰሰባቸውን ጥናቶች የመደርደሪያ ማሞቂያ ከመሆን ወጥተው የጥናቱ ውጤት ታይቶ የሚታረመው እንዲታረም፤ የሚገሰጸው እንዲገሰጽ መሠራት እንዳበት አሳስበዋል፡፡ ‹‹ጥናቶቹን በአግባቡ መርምሮ የሚያያቸው የለም እንጂ እንደ አገር ብዙ ብክነቶችን ልንከላከልባቸው እንችል ነበር፡፡ አሁንም ቢሆን አልረፈደም የተጠኑትን ጥናቶች በመተግበር የአዲስ አበባ መስተዳድር ምክር ቤት አባላት እና ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር በመተባበር ለመሥራት ተዘጋጅተናል›› ብለዋል ምክትል ኮሚሽነሩ፡፡
[ 107 ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራር" ]
[ "ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ስለተወሰዱ እርምጃወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት፡፡" ]
[ "ስለ ሙስና እና ብልሹ ስራወች ምን ምን እነደሆኑ, ሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ መንገዶች, የግዛቤ ማስጨበጫ ስለጠናወች ጠቃሚ የመረጃ ምነጮች ናቸው፡፡ ስለ ሙስና ክሶች የሚያትቱ ሰነዶች ጠቃሚወች አይደሉም፡፡" ]