input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
በተቃራኒዉ ከጋና በርካታ ወጣቶች ለትምህርትም ሆነ ለሙያዊ ሥልጠና ወደ ጀርመን እንዲመጡ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ እንፈልጋለን።
|
ሕገወጥ ስደተኝነትን መዋጋት ይኖርብናል ሆኖም በአንፃሩ ለወጣቶች ሕጋዊ ዕድሎች እንዲከፈቱ እንፈልጋለን።
|
ጀርመን ዉስጥ በአሁን ወቅት ወደጋና ሊመለሱ ይችላሉ የተባሉ አራት ሺህ ገደማ ተሰዳጆች ይኖራሉ።
|
የተመላሽ ስደተኞችን ሁኔታ ለማመቻቸትም አክራ ላይ በጀርመን ትብብር አንድ ማዕከል ተከፍቷል።
|
እንዲያም ሆኖ የጋናዉ ፕሬዝደንት ወደጋና ይመለሳሉ የተባሉት ማንነት አስቀድሞ እንዲጣራ ጠይቀዋል።
|
መዝናኛ፦ አዝማሪ ከያንያን ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
የቱርክ ሕዝበ ውሳኔ ውጤት ባለፈው እሁድ ቱርክ ያካሄደችው ህዝበ ውሳኔ የቱርክ ፕሬዝዳንት ጠይብ ሬቼፕ ኤርዶሃን የሚፈልጉትን ውጤት አስገኝቷል ።
|
ድምጽ ለመስጠት ከወጣው ህዝብ በመቶው በቱርክ ህገ መንግሥት ላይ ማሻሻያ እንዲደርግ ተስማምቷል።
|
ማሻሻያው የቱርክን አስተዳደር ከፓርላሜንታዊ ወደ ፕሬዝዳንታዊ የመንግሥት ስርዓት የሚቀይር ነው ።
|
ፕሬዝዳንቱ ቀድሞ ያልነበረውን ሚኒስትሮች የመሰየም በጀት የማዘጋጀት እና አብዛኛዎቹን ከፍተኛ ዳኞች የመሾም ሥልጣን ያገኛል።
|
በመቶ ድምፅ ሰጭዎች ማሻሻያው ፕሬዝዳንቱ ሥልጣኑን በሙሉ ጠቅለው እንዲይዙ ስለሚያደርግ ህገ መንግሥቱ እንዳለ ይቀጥል ሲሉ ነበር ድምጻቸውን የሰጡት ።
|
ከዚህ ሌላ ህዝቡ ስለ ህዝበ ውሳኔው ምንነት አስቀድሞ በቂ መረጃ እንዲያገኝ አልተደረገም ሲሉም ተችተዋል።
|
በህገ መንግሥታዊ ማሻሻያ ጥያቄ ላይ የተካሄደው የሚያዚያ ቱ ህዝበ ውሳኔ በተመጣጣኝ የመፎካከሪያ ሜዳ ላይ አልተካሄደም ።
|
ድምጽ ሰጭዎች ስለ ማሻሻያው ቁልፍ ጉዳዮች ገለልተኛ የሆነ መረጃ አልተሰጣቸውም።
|
በሐምሌ ከከሸፈው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኋላ የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለዴሞክራሲያዊ ሂደት ወሳኝ የሆኑ መሠረታዊ ነጻነቶችን ገድቧል።
|
ቱርክን ከአውሮጳ ህብረት ጋር ካቃቃሯት ጉዳዮች አንዱ የአውሮፓ ህብረት አባል ለመሆን ስታካሂድ የነበረው ድርድር መገታት ነው።
|
ህብረቱ ሀገሪቱ ማሟላት አለባት የሚላቸውን በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ያተኮሩ መስፈርቶችን ለድርድሩ አለመቀጠል አንደ አንድ ምክንያት ይጠቀሳል።
|
የዶቼቬለ የኢስታንቡል ዘጋቢ ዶርያን ጆንስ እንዳለው የአውሮጳ ታዛቢዎች አስተያየት እና የኤርዶሀን ዛቻ በድርድሩ ተስፋ ላይ ተጽእኖ ማሳደሩ አይቀርም።
|
የአውሮጳ ምክር ቤት እና ኦ ኤስ ሲ ኢ ህዝበ ውሳኔው የተካሄደበትን መንገድ በጥብቅ አውግዘዋል።
|
እናም ቱርክ ኤርዶጋን በሥልጣን ላይ እስካሉ ድረስ የአውሮጳ ህብረት ህብረት አባል መሆን አትችልም የሚለው አስተሳሰብ በአውሮፓ እንዲሰፍን አድርጓል ።
|
እንደሚመስለኝ ከአውሮጳ ህብረት ጋር ስታካሂድ የቆየችው ድርድር ወደፊት የመራመዱ ተስፋ አናሳ ነው ።
|
የጀርመን ጥምር መንግሥት አካል የሆነው የክርስቲያን ሶሻል ህብረት ፓርቲ በምህፃሩ ሊቀመንበር ማንፍሬድ ቬበር ይህን ካሉት የጀርመን ፖለቲከኞች አንዱ ናቸው።
|
ቱርክ አሁን በአውሮጳ ህብረት እይታ የተሳሳተ መንገድ ለመከተል ከመረጠች ከቱርክ ጋር ያለንን ግንኙነት እንደገና መፈተሽ አለብን ።
|
ያ ማለት በቱርክ የአውሮጳ ህብረት አባልነት ማመልከቻ ላይ የምናካሂደው ድርድር በረዥሙ ጊዜ ሊቀጥል አይችልም።
|
ለንግግር መቅረብ ያለበት የሁለቱንም ወገኖች ጥቅም የሚያስጠብቅ አጋርነት ነው።
|
ይህን መታዘቡን ያሳወቀው የጀርመን መንግሥት ክፍፍሉን ለማስወገድ በቱርክፖለቲካዊ ውይይት እንዲካሄድ ጠይቋል።
|
ይሁንና እና ፕሬዝዳንት ኤርዶሀን ከድሉ በኋላ ትናንት ባሰሙት ንግግር ማሳሰቢያዎቹን ከቁብ የቆጠሩት አይመስልም ።
|
ስለ ህዝበ ውሳኔው የሚደረገው ውይይትም ሆነ ውዝግቡ አብቅቷል ትችቱም መቆም አለበት ብለዋል ።
|
የህዝበ ውሳኔው ውጤት የተቃወሙትንም ተመልከቱ እንዴት ሽንፈታቸውን እንደሚያከበሩ ሲሉ አሹፈውባቸዋል።
|
ምንም እንኳን ከአንድ በመቶ በላይ በሆነ ድምጽ ቢያሸንፉም ትችቱ መቆም አለበት የሚል እምነት ነው ያላቸው።
|
እናም ፕሬዝዳንቱ በተቃዋሚዎች ላይ ጠንከር ያለ እርምጃ ይወስዳሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው።
|
ጋዜጠኛ ዲርያን እንደሚለው ኤርዶሀን ከሁለት ዓመት በኋላ ማለትም በጎርጎሮሳዊው በቱርክ ለሚካሄደው ምርጫ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ከአሁን መንገዱን እያመቻቹ ነው።
|
ፀረ አውሮጳ ንግግራቸውም ሆነ ዛቻቸው በህዝበ ውሳኔ ያጡትን ድምጽ ለማግኘት የሚጠቀሙበት ዘዴም ነው ይላል።
|
ከቱርክ ብሔረተኞች አብዛኛዎቹ በህዝበ ውሳኔው ልደገፏቸውም የሚል ግምት አለ ።
|
በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ በሚካሄደው ምርጫ ኤርዶሀን የብሔረተኞች ድምጽ ያስፈልጋቸዋል ።
|
እናም የሞት ቅጣት ተመልሶ ህጋዊ ይሁን አይሁን የሚለው ጉዳይ እና በአውሮጳ ህብረት ላይ የሚያነሱት ጥያቄ የብሔረተኞችን ቀልብ ለመሳብ ይጠቅማቸዋል ።
|
ግን ጥያቄው እነዚህ ጉዳዮች ለህዝበ ውሳኔ ይቀርባሉ ወይ ነው ።
|
ከአውሮፓ ምክር ቤትም ሆነ ከአውሮፓ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤትጋር የሚኖራት ግንኙነትም ጥያቄ ውስጥ ይገባል።
|
ስደተኞች ወደ አውሮጳ እንዳይገቡ ለመከላከል ከህብረቱ ጋር የደረሰችበት ውል ሁለቱን ወገኖች ከሚያስተሳስሯቸው ጥቅሞች አንዱ ነው ።
|
ቱርክ የአውሮፓ ህብረት ዋነኛ የንግድ አጋር መሆንዋም ሌላው የጋራ ጥቅማቸው መገለጫ ነው።
|
የነዚህ ትስስሮች የወደፊት እጣ ምን ሊሆን ይችላል የሚለው አሁንም ማነጋገሩ እንደቀጠለ ነው።
|
የኢትዮጵያ መንግስት የቀድሞውን የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝዳንት በአዲስ አበባ እንዳይተላለፉ ያገደው ባለፈው እሁድ ነበር፡፡
|
የስፖርት ዘገባ ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ሩስያን በተመለከተ ትናንት ያስተላለፈው ውሳኔ ብዙዎችን አስደምሟል።
|
የሩስያ መንግሥት አትሌቶቹ አበረታች ንጥረ ነገሮችን እንዲጠቀሙ ሁኔታዎችን ሲያመቻች በመክረሙ ቡድኑ ሙሉ ለሙሉ ከሪዮ ኦሎምፒክ ሊታገድ ይችላል ተብሎ ነበር።
|
የቱር ደ ፍሯንስ ብስክሌት ሽቅድምድም በብሪታንያዊው ክሪስ ፍሮም ድል ተጠናቋል።
|
በሜዳ ቴኒስ የሞንትሪያል ውድድር ሴሬና ዊሊያምስ ለሦስት ጊዜያት ያሸነፈችበት ውድድር ላይ አትካፈልም።
|
የአውስትራሊያ የኦሎምፒክ ቡድን ወደ ሪዮ የኦሎምፒክ መንደር እንደማይገባ አስታወቋል።
|
በፖላንዱ ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች አትሌቲክስ ፉክክር ኢትዮፕያ የሦስተኛ ደረጃን አገኘች።
|
ዓለም አቀፉ የኦሎምፒክ ኮሚቴ ሩስያ ሙሉ ለሙሉ ከሪዮ ኦሎምፒክ ትታገድ የሚለውን ሐሳብ ውድቅ አድርጓል።
|
ሐሳቡ የቀረበው በዓለም አቀፉ ጸረ አበረታች ንጥረ ነገር ተከታታይ ተቋም በእንግሊዝኛ ምኅጻሩ ነበር።
|
እያንዳንዱ አትሌት በውድድሩ ላይ መሳተፍ አለያም አለመሳተፉን በተመለከተ ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች በተናጠል ሊወስኑ ይችላሉ ብሏል።
|
ብዙአየሁ ዋጋው የዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማኅበርን ጨምሮ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ መገናኛ አውታሮች ዘጋቢ ነው።
|
በሩስያ ጉዳይ ዓለም አቀፍ የስፖርት ተቋማቱ ወዲህ እና ወዲያ የማለታቸውን ምክንያት እንዲህ ያብራራል።
|
ይህን የተናገሩት የሩስያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ኃላፊ አሌክሳንደር ዙኮቭ መሆናቸውን አር ስፖርት የዜና ምንጭ ዘግቧል ሲል ሮይተርስ አክሎ ጠቅሷል።
|
በፖላንድ ቢድጎቺች ከተማ ለ ቀናት የተከናወነው የታዳጊዎች የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ትናንት ተጠናቋል።
|
ዕድሜያቸው ከ ዓመት በታች የሆኑ አትሌቶች በሚሳተፉበት ውድድር ኢትዮጵያ የወርቅ የብር እና የነሀስ በአጠቃላይ ሜዳሊያዎችን በማግኘት ኬንያን ተከትላ ሦስተኛ ወጥታለች።
|
የወርቅ የብር እና የነሀስ በአጠቃላይ ሜዳሊያዎች ሰብስባ ዩናይትድ ስቴትስ አንደኛ ወጥታለች።
|
ስዋንሲ ሲቲ ደግሞ የ ዓመቱ ዊልፍሬድ ቦኒን ከማንቸስተር ሲቲ ሊያስፈርም እየተነጋገረ መሆኑን ሰንዴይ ኤክስፕረስ የተሰኘው ጋዜጣ አትቷል።
|
ቸልሲ በቅርቡ ያስፈረመው ንጎሎ ካንቴ በሚቀጥለው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ የሚለብሰው ሰባት ቁጥር መለያ ሰጥቶታል።
|
የማርሴዩ የክንፍ ተጨዋች ጌኦርጌስ ኬቪን ንኮዱ ለቶትንሀም ለመፈረም ጫፍ ላይ መድረሱን ኢንዲፔንደት ዘግቧል።
|
ሊቨርፑል ለአውሮጳ ሊግ ከስፔኑ ሴቪያ ጋር በተጫወተበት ወቅት ደጋፊዎቹ ርችቶችን እየተኮሱ በመበጥበጣቸው ፓውንድ መቀጣቱ ተገልጧል።
|
የደጋፊዎች ብጥብጡ የተከሰተው ከሁለት ወራት በፊት የስዊዘርላንድ ባዝል ከተማ ውስጥ ነበር።
|
ብስክሌት ብሪታንያዊው ክሪስ ፍሮም በቱር ደ ፍሯንስ የብስክሌት ሽቅድምድም ኛ እና የመጨረሻ ዙር ውድድር አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ።
|
ክሪስ ዘንድሮ የውድድሩ አጠቃላይ አሸናፊ ሲሆን ለሦስተኛ ጊዜ ነው።
|
አሜሪካዊው ላንስ አርምስትሮንግ ውጤቶቹን በመነጠቁ ክሪስ ፍሮም ከስፔናዊው ሚጉዌል ኢንዱራይን ቀጥሎ ውጤቱን በማስጠበቅ ሁለተኛ ነው።
|
ለ ተከታታይ ጊዜያት አሸናፊ የነበረው አሜሪካዊው ላንስ አርምስትሮንግ አጠቃላይ ውጤቶቹ የተሰረዙበት አበረታች ንጥረ ነገር መጠቀሙን በማመኑ ነበር።
|
ስፔናዊው ሚጉዌል ኢንዱራይንእንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር ከ አንስቶ ለአምስት ተከታታይ ዓመታት የቱር ደ ፍሯንስ የብስክሌት ሽቅድምድም አሸናፊ ጠንካራ ተወዳዳሪ ነው።
|
የዘንድሮውን ጨምሮ ለሦስት ዓመታት ባለድል የሆነው የብሪታንያው ክሪስ ፍሮሜሚጉዌል ላይ ለመድረስ እየገሰገሰ ነው።
|
ምናልባት ጥንካሬው በዚሁ ከቀጠለ እና በተከታታይ ካሸነፈ በ ዓመቱ ስፔናዊውን በመብለጥ ክብርወሰኑን ይሰብር ይሆናል።
|
ለ የተለያዩ ቀናት በተከናወነው የቱር ደ ፍሯንስ የብስክሌት ሽቅድምድም አጠቃላይ ውጤት ኢትዮጵያዊው ጽጋቡ ገብረማርያም ከ ተወዳዳሪዎች የ ኛ ደረጃን አግኝቷል።
|
ጽጋቡ ለመጀመሪያ ጊዜ በቱር ደ ፍሯንስ ያስመዘገበው ውጤት እጅግ የሚበረታታ ነው።
|
የኤርትራው ናትናኤል ብርሃኔ ኛ ደረጃን ሲያገኝ ሌላኛው የኤርትራ ተወዳዳሪ ዳንኤል ተክለ ሃይማኖት ኛ በመውጣት ጠንካራ ብስክሌተኛነቱን አስመስክሯል።
|
ሴሬና ከውድድሩ የወጣችው ትከሻዋ ላይ በደረሰባት ጉዳት መሆኑን የውድድሩ አዘጋጆች ገልጠዋል።
|
በእሁዱ የሐንጋሪ ግራንድ ፕሪ ሽቅድምድም ሐሚልተን ሰአት ከ ደቂቃ ከ ሰከንድ በማጠናቀቅ መሪነቱን አስጠብቋል።
|
በፌራሪ ተሽከርካሪው የሚወዳደረው የፊንላንዱ አሽከርካሪ ኪም ሬይከነን በ ነጥቡ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
|
አሜሪካዊቷ ሴሬና ዊሊያምስ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የስደተኞች ቡድን በኦሎምፒክ ይሳተፋል።
|
በስደተኞች ቡድን ከታቀፉት አትሌቶች መካከል የ ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ማራቶን ሯጭ ዮናስ ኪዳኔ ይገኝበታል።
|
ዮናስ ካለፉት አምስት ዓመታት አንስቶ ነዋሪነቱን በአውሮጳ ሉግዘምበርግ አድርጓል።
|
ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ ጀርመን ውስጥ ያደረገውን ውድድርም ሰአት ከ ደቂቃ በማጠናቀቅ ብርቱ ተፎካካሪ መሆኑን አሳይቷል።
|
የአውስትራሊያ የኦሎምፒክ ቡድን የብራዚሏ ሪዮ የኦሎምፒክ መንደር የጥራት ደረጃውን የጠበቀ አይደለም በሚል አትሌቶቹ መንደሩ ውስጥ እንደማይቆዪ አስታወቀ።
|
ፍሳሽ በአግባቡ የማያስተላልፉ መጸዳጃ ቤቶች እና የሚያንጠባጥቡ ቧንቧዎች መገኘታቸው አውስትራሊያ ወደ ኦሎምፒክ መንደሩ ላለመሄድ ምክንያት እንደሆናት አስታውቃለች።
|
ከ ዓመት በታች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የፍጻሜ እና የደረጃ ውድድሮች የፊታችን ቅዳሜ እንደሚከናወኑ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በኢሜል በላከው መልእክት ገልጧል።
|
የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቀድሞው ፕሬዚዳንት ቮልፍጋንግ ኒርስባኅ ከማንኛውም የእግር ኳስ እንቅስቃሴ ለአንድ ዓመት ታገዱ።
|
ሆኖም አብዛኛዎቹ ጀርመን እንድትቀበላቸው የጠየቁ አመልካቾች የመኖሪያ ፈቃድ የማግኘት እድላቸው አነስተኛ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ባለሞያዎች ይናገራሉ ።
|
ጀርመን ውስጥ ካለ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሰቀቀን ህይወት በመግፋት ላይ የሚገኙም ጥቂት አይደሉም ።
|
ለዚህም ድርጅቱ በዋነኛ ምክንያትነት ያቀረበው የሶሪያውን የርስ በርስ ጦርነት ነው ።
|
ከሶሪያና ከሌሎች ሃገራት ተሰደው በ በኢንዱስትሪ በበለፀጉት ሃገራት ጥገኝነት እንዲሰጣቸው ያመለከቱ ስደተኞች ቁጥር ከ ሺህ በላይ ነው ።
|
በዓመቱ ጀርመን ጥገኝነት እንዲሰጣቸው ያመለከቱ ስደተኞች ወደ ሺህ ይጠጋሉ ።
|
ዩናይትድ ስቴትስ ሁለተኛውን ደረጃ ስትይዝ የጥገኝነት ማመልከቻ ያስገቡት ቁጥር ሺህ ነው ።
|
የጀርመን የተገን አሰጣጥ ሂደት ቢያንስ አንድ ዓመት ወይም ደግሞ ከዚያ በላይ የሚወስድ በመሆኑ ከአመልካቾቹ ምን ያህሉ ጀርመን እንደሚቆዩ አይታወቅም ።
|
የአብዛኛው ተገን ጠያቂዎች ምርጫ ጀርመን የሆነበት ምክንያት እያነጋገረ ነው ።
|
አብዛኛዎቹ በሌላ የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገር የተመዘገቡ ናቸው ።
|
እዚያም አብዛኛዎቹ ተገን ጠያቂዎች እስከመኖራቸው የተረሱ በአግባቡም ያልተያዙና የሃገራቱ ስደተኞች አቀባበል ስርዓት የተከተለ አይደለም ።
|
ከምክንያቶቹ አንደኛው በአውሮፓ ህብረት ህግ መሰረት አንድ ተገን ጠያቂ ጉዳዩ መታየት ያለበት መጀመሪያ በገባበት ሃገር መሆኑ ነው ።
|
የጀርመን የውጭ ዜጎችና የስደተኞች ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጀርመን እንድትቀበላቸው የሚያመለክቱ ተገን ጠያቂዎችን ወደ መጡበት ለመመለስ የተቻለውን ሁሉ ይሞክራል ።
|
በተለይ የተሻለ አያያዝ አላቸው ተብለው ከሚታሰቡት ሃገራት የሚመጡት ሰዎች ማመልከዎች ተቀባይነት ያለማግኘት እድላቸው ከፍተኛ ነው ።
|
በሜሶቪክ እምነት በ ጀርመን ከደረሷት ሺህ የተገን ጠያቂዎች ማመልከቻዎች አብዛኛዎቹ በቀደመው በ ዓም ጥያቄአቸው ውድቅ የተደረገባቸው ስደተኞች ማመልከቻዎችም ናቸው ።
|
ጥቂት የማይባሉም የፖለቲካ ጭቆና ወይም ኢሰብዓዊ ቅጣቶች አይፈፀሙባቸውም ለህይወት አስጊ አይደሉም ከሚባሉ የባልካን አገራት ነው የመጡት ።
|
የጀርመን መንግሥት ከነዚህ ሃገራት የሚሰደዱትን ሰዎች ማመልከቻቸውን በቀላሉ ውድቅ ለማድረግ የሚረዳውን ህግ እያረቀቀ ነው ።
|
አሁን የፌደራል ጀርመን መንግስት ከምዕራብ ባልካን ሃገራት የመጡ ስደተኞች ላስገቧቸው የጥገኝነት ማመልከቻዎች መልስ መስጠት የሚችልበትን ረቂቅ ህግ እያዘጋጀ ነው ።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.